ኢዜአ - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ በሱዳን ያለው ግጭት በሰላም እንዲቋጭ የሚደረገውን ጥረት በፅኑ ትደግፋለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Dec 9, 2023 54
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ በሱዳን ያለው ግጭት በሰላም እንዲቋጭ የሚደረገውን ጥረት በፅኑ ትደግፋለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ወንድሜ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ በሱዳን ጉዳይ ላይ የተካሄደውን 41ኛውን የኢጋድ ልዩ የመሪዎች ጉባኤ በማስተናገዳቸው ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ባወጣው መረጃ ደግሞ ኢትዮጵያ በኢጋድ የሚደረገውን የሰላም እና መረጋጋት ሂደት በንቃት በመደገፍ ላይ መቆየቷ አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩና የልኡካን ቡድናቸው ተሳትፏቸውን አጠናቀው ዛሬ ማምሻውን ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸውንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ ውድድር በትንሿ ስቴድየም ተጀመረ
Dec 9, 2023 39
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ ውድድር በትንሿ ስቴድየም በዛሬው ዕለት ተጀምሯል። በአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ( ቮሊቦል) ፌዴሬሽን አማካኝነት በተዘጋጀው በዚህ ውድድር በወንዶች አምስት ክለቦች በሴቶች አራት ክለቦች የሚሳተፉበት ሲሆን እስከ ታህሳስ 14 ቀን 2016 ዓ.ም ይቆያል። በውድድሩ ማስጀመሪያ በወንዶች መቻል ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር ተጫውተው አዲስ አበባ ፖሊስ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል። በሴቶች ፌደራል ማረሚያ ቤት አዲስ ከተማን 3 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል። የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳዊት ትርፉ ተወዳጅ የሆነውን የመረብ ኳስ ስፖርት ለማስፋፋት ቢሮው በቀጣይም ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል። ዛሬ የተጀመረው ውድድር አዲስ አበባን ወክለው በሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ መድረክ ላይ የሚሳተፉ ስፖርተኞችን ለማፍራት እንደሚያስችል ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ በላይነህ ተካ በበኩላቸው የክለቦች የመረብ ኳስ ውድድር ለረዥም ጊዜ ሳይካሄድ ቆይቶ እንደነበር አስታውሰዋል። የውድድሩ ቀጣይነትም በከተማ ደረጃ የመረብ ኳስ ስፖርት እንዲያድግ እና ለፕሪሚየር ሊግ አቅም የሚሆኑ ልጆችን ለማግኘት ስፖርቱ ሊጠናከር ይገባል ብለዋል። በመረብ ኳስ (ሲቲካፕ) ውድድሩ በሴቶች ጌታ ዘሩ፣ ፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን፣ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማና ብሔራዊ አልኮል ይወዳደራሉ። በወንዶች ደግሞ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ አቃቂ ክፍለ ከተማ፣ ብሔራዊ አልኮል፣ መቻል እና አዲስ አበባ ፖሊስ በውድድሩ እንደሚካፈሉ የአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያየ
Dec 9, 2023 42
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29 /2016 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአፍሪካ እና በመካለኛው ምስራቅ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር የበይነ መረብ ውይይት አደረገ ፡፡ የውይይት መድረኩ የዲያስፖራው ማህበረሰብ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ንቁ ተሳትፎና ድጋፍ እንዲያደርግ ግንዛቤን መፍጠር ያለመ መሆኑ ተመላክቷል ፡፡ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፈን አርአያ ባደረጉት የውይይቱ መክፈቻ ንግግር ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተመካክሮ መግባባት ለሀገራችን መጻኢ ተስፋ እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል ፡፡ በውይይቱ ስለ ሀገራዊ ምክክሩ መሰረታዊ ፅንሰ-ሀሳቦች ፣ በኮሚሽኑ ስለተከናወኑ አንኳር ተግባራት እና ኮሚሽኑ ስለሚገዛባቸው የህግ ማዕቀፎች ማብራርያ ተሰጥቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኮሚሽኑ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የዲያስፖራ አባላት ጋር በትብብር ስለሚሰራባቸው መንገዶች ላይ ሀሳብ እና አስተያየቶች በውይይቱ ቀርበዋል፡፡ በመጪዎቹ ጊዜያት ኮሚሽኑ መሰል ውይይቶችን በሌሎች የዓለማችን ክፍሎች ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በማድረግ ለሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን እንደሚሰበሰብ ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማህበራዊ ድኅረ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ በሚያደርግልን ድጋፍ የተረጋጋ ህይወት እየመራን ነው - ስደተኞች
Dec 9, 2023 45
ጎንደር ፤ ህዳር 29 /2016 (ኢዜአ) ፡- የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ በሚያደርግልን ድጋፍ የተረጋጋ ኑሮ ለመምራት ችለናል ሲሉ በዳባት አለም ዋጭ የስደተኞች መጠለያ የሚገኙ የጎረቤት አገር ስደተኞች ተናገሩ፡፡ ስደተኞቹ የዳባትና አካባቢው ማህበረሰብ ባለፉት አራት ወራት ላደረገላቸው ሰብአዊ ድጋፍ የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ዛሬ በመጠለያው አካሂደዋል፡፡ የስደተኞች ተወካይ አቶ ሰለሞን ተስፋማርያም በስነ ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ መንግስትና የዳባት አካባቢው ህዝብ ባለፉት አራት ወራት አለም አቀፍ ረጅ ድርጅቶች እርዳታ ባቋረጡበት ወቅት ያደረጉላቸው ድጋፍና እንክብካቤ በታሪክ ሲታወስ የሚኖር ነው። የምግብ እህልና ሌሎች ሰብአዊ ድጋፎችን በመጠለያው ለሚገኙ ስደተኞች በማቅረብ የመደጋገፍና የመተሳሰብ ጥልቅ ማህበራዊ እሴታቸውን በተግባር አሳይተውናል ሲሉ ገልጸዋል። "ከአገሬ ኤርትራ ተሰድጄ ከመጣሁ ጀምሮ የአካባቢው ማህበረሰብ ከአቀባበል ጀምሮ ያደረጉልን ድጋፍ ኢትዮጵያን እንደ ሀገሬ እንድመለከት አድርጎኛል" ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ፊወሪ እቁባይ ናቸው፡፡ "ማህበረሰቡ ለስደተኞች የሚያደርገው እገዛና እንክብካቤ ፍጹም ያለስጋት የተረጋጋ ህይወት እንድንኖር አድርጎናል" ያሉት ወይዘሮ ፊወሪ፤ እርዳታ በተቋረጠበት ወቅት ለእኛንና ለልጆቻችን የተለየ ድጋፍ በማድረግ ተንከባክበውናል ብለዋል፡፡ ሌላዋ ስደተኛ ወይዘሮ ዮዲት አጽብኃ ፤ የአካባቢው ማህብረሰብ ለስደተኛው የሚያሳየው ፍቅርና መተሳሰብ ወንድማማችነትንና አብሮነትን የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል። የሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር ተወካይ አቶ አስማረ አበራ በእለቱ እንዳሉት ፤ ስደተኞቹ መብታቸው ተከብሮ ሰላማዊና የተረጋጋ ህይወት እንዲመሩ በማድረግ ረገድ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ስራ ተከናውኗል፡፡ የዞኑ አስተዳደር በዳባት ከተማ 90 ሄክታር የሚሸፍን መሬት ለስደተኛ መጠለያ ቦታ በማዘጋጀት ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ መደገፉን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም በስደተኞቹና የአካባቢው ማህብረሰብ ያለውን ግንኙነት ከመደገፍ የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች አገልግሎቶችን እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመጠለያ ጣቢያው ከ20ሺህ በላይ የጎረቤት ሀገር ስደተኞች እንደሚገኙ የገለጹት ደግሞ የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት የዳባት አለምዋጭ ስደተኛ መጠለያ አስተባባሪ አቶ ታምራት ደምሴ ናቸው፡፡ ለስደተኞቹ ይቀርብ የነበረው የምግብ እህል አቅርቦት ላለፉት አራት ወራት ተቋርጦ መቆየቱን ያስታወሱት አቶ ታምራት፤ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱ ዳግም መጀመሩን ገልጸዋል፡፡ የምግብ አህል አቅርቦቱ በተቋረጠበት ወቅት የአካባቢው ማህበረሰብ ስደተኞቹ ችግር እንዳይገጥማቸው በማሰብ ያልተቋረጠ የምግብ እህል ድጋፍ በማድረግ የጸና ፍቅሩን በተግባር ማረጋገጡን አንስተዋል፡፡ በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ የዞንና የወረዳ አመራር አባላት ፣ የአካባቢው ማህበረሰብና የስደተኞች ተወካዮች በተገኙበት በድጋፉ የነቃ ተሳትፈ ላበረከቱ ግለሰቦችና ድርጅቶች እውቅና ተሰጥቷል፡፡
የአክሱም ዩኒቨርሲቲ 1 ሺህ 692 አዲስ ተማሪዎችን ተቀበለ
Dec 9, 2023 38
መቀሌ፤ ህዳር 29/2016(ኢዜአ)፡- የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡለትን 1 ሺህ 692 አዲስ ተማሪዎች መቀበሉን አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙሉጌታ በሪሁ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሚያስተምራቸውን ተማሪዎች የተቀበለው ባለፉት ሁለት ቀናት ነው። ዩኒቨርሲቲው ከተቀበላቸው ተማሪዎች መካከል 635ቱ ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል ። ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎቹን ተቀብሎ የመማር ማስተማር ሥራውን ለማካሄድ የመኝታ፣የመማሪያና የመመገቢያ ክፍሎች ዝግጅት ማድረጉን አስረድተዋል። እንዲሁም የቅጥር ግቢውን ጽዳትና የጥገና ሥራዎች አከናውኗል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው ትምህርታቸውን በተለያዩ ምክንያቶች አቋርጠው የነበሩ 4 ሺህ 122 ተማሪዎች ተቀብሎ እያስተማረ መሆኑንም ዶክተር ሙሉጌታ ገልጸዋል። የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ከተቋቋመ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት መስኮች አስተምሮ ማስመረቁን መረጃዎች ያመለክታሉ። መቀሌ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡለትን ከአንድ ሺህ በላይ የተፈጥሮና የማህበረሰብ ሳይንስ ተማሪዎችን መቀበል እንደጀመረ ትናንት መዘገባችን ይታወሳል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በሱዳን ያለው ግጭት በሰላም እንዲቋጭ የሚደረገውን ጥረት በፅኑ ትደግፋለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Dec 9, 2023 54
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ በሱዳን ያለው ግጭት በሰላም እንዲቋጭ የሚደረገውን ጥረት በፅኑ ትደግፋለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ወንድሜ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ በሱዳን ጉዳይ ላይ የተካሄደውን 41ኛውን የኢጋድ ልዩ የመሪዎች ጉባኤ በማስተናገዳቸው ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ባወጣው መረጃ ደግሞ ኢትዮጵያ በኢጋድ የሚደረገውን የሰላም እና መረጋጋት ሂደት በንቃት በመደገፍ ላይ መቆየቷ አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩና የልኡካን ቡድናቸው ተሳትፏቸውን አጠናቀው ዛሬ ማምሻውን ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸውንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያየ
Dec 9, 2023 42
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29 /2016 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአፍሪካ እና በመካለኛው ምስራቅ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር የበይነ መረብ ውይይት አደረገ ፡፡ የውይይት መድረኩ የዲያስፖራው ማህበረሰብ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ንቁ ተሳትፎና ድጋፍ እንዲያደርግ ግንዛቤን መፍጠር ያለመ መሆኑ ተመላክቷል ፡፡ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፈን አርአያ ባደረጉት የውይይቱ መክፈቻ ንግግር ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተመካክሮ መግባባት ለሀገራችን መጻኢ ተስፋ እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል ፡፡ በውይይቱ ስለ ሀገራዊ ምክክሩ መሰረታዊ ፅንሰ-ሀሳቦች ፣ በኮሚሽኑ ስለተከናወኑ አንኳር ተግባራት እና ኮሚሽኑ ስለሚገዛባቸው የህግ ማዕቀፎች ማብራርያ ተሰጥቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኮሚሽኑ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የዲያስፖራ አባላት ጋር በትብብር ስለሚሰራባቸው መንገዶች ላይ ሀሳብ እና አስተያየቶች በውይይቱ ቀርበዋል፡፡ በመጪዎቹ ጊዜያት ኮሚሽኑ መሰል ውይይቶችን በሌሎች የዓለማችን ክፍሎች ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በማድረግ ለሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን እንደሚሰበሰብ ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማህበራዊ ድኅረ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበር ህዝቦች ይበልጥ እንዲተዋወቁ ማስቻሉን የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ገለጹ
Dec 9, 2023 47
መቱ/ ነቀምቴ፤ሕዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፦ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበር ህዝቦች ይበልጥ እንዲተዋወቁ፣ አንድነትና ወንድማማችነት እንዲጠናከር እድል እየፈጠረ ነው ሲሉ የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተናገሩ። የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የዘንድሮውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ባከበሩበት ወቅት በዓሉ የሕዝቦችን ወንድማማችነት እያጠናከረ ነው ብለዋል። ተማሪ ኬን ኩዌስ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበር ዜጎች ይበልጥ እንዲተዋወቁና እንዲከባበሩ እድል ፈጥሯል ብላለች። ''ከሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች መጥተን ተከባብረንና ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን ጠብቀን እየተማርን ነው'' ያለቸው ተማሪ ኬን ''በዓሉ አንድነታችንን ለማጠናከር አግዞናል'' ስትልም ገልጻለች። ተማሪ ፈትያ መኪ ሰይድ በበኩሏ ለኢትዮጵያ ሰላምና ዕድገት እውን መሆን ለልዩነቶቻችን እውቅና የመስጠት እንዲሁም የመከባበር፣ አብሮነትን ማጎልበት ይገባል ብላለች። ለዚህ ደግሞ እንደ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን ያሉ የጋራ ጉዳዮቻችንን ማሳደግ የሚያችሉ መድረኮች ወሳኝና ይበልጥ የመተዋወቂያና መቀራረቢያ መድረኮች መሆናቸውን ተናግራለች። ዩኒቨርሲቲዎች ከተለያዩ የብሔር፣ የቋንቋ፣ የኃይማኖትና ሌሎች ብዝኃነቶች የመጡ ተማሪዎች ለዓመታት በጋራ የሚቆዩበት እንደመሆኑ ለኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት መጎልበት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የተናገረችው ደግሞ ተማሪ ሲፈን ድሪባ ናት። በተለይ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መከበሩ ትልቅ ትስስር የሚፈጥር መሆኑን ተናግራለች። የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረት ፕሬዚዳንት ተማሪ ኩምሳ ታምሩ በበኩሉ ''በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ልዩነቶቻችንን አክብረንና አንድነታችንን ጠብቀን የምናሳልፈው ጊዜ ለኢትዮጵያዊ አንድነት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው'' ብሏል። የብሔር ብሕረሰቦች ቀን መከበሩ ለእኩልነት፣ ለአንድነት፣ ለአብሮነት፣ ለትውውቅና ለወንድማማችነት መጠናከር ትልቅ ዕድልን የፈጠረ ነው ሲልም አክሏል። በተመሳሳይ የወለጋ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ የአስተዳደር ሰራተኞች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዓሉን አክብረዋል። የበዓሉ ተሳታፊ ተማሪዎች፣ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ውበታችንን የምናጎላበትና አንዱ ሌላው የሚያውቅበት ነው ብለዋል። ተማሪ ገመቺስ ታከለ፣ የሌላውን ማንነት ማክበር ራስን ማስከበር መሆኑን ገልጻ ሁሉም ተቻችሎ እና ተከባብሮ አገሩን ማሳደግ አለበት ብላለች። ተማሪ መለሰ ያእቆብ በዩኒቨርሲቲው እርስ በርስ ተከባብረው ያለችግር ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ ገልጿል። የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሀሰን ዩሱፍ፣ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበር እኩልነትና ብዝሃነት ማስተዋወቅ መሆኑን አስረድተዋል። የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብም በፍቅርና በመከባበር የተሻለ ዜጋ የማፍራቱን ስራ ማጠናከር እንዳለባቸው አሳስበዋል። በወለጋ ዩኒቨርስቲ 18ኛው የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ላለፉት አምስት ቀናት በተለያዩ ፕሮግራሞች ሲከበር መቆየቱም ታውቋል።
በጅግጅጋ ከተማ ሲከበር የነበረው 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በሰላም ተጠናቀቀ
Dec 9, 2023 70
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፡- በጅግጅጋ ከተማ በድምቀት ሲከበር የነበረው 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በሰላም መጠናቀቁን የሶማሌ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል። የሶማሌ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ ፈርሃን ጅብሪል ለኢዜአ እንደገለጹት 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ለተከታታይ ቀናት በጅግጅጋ ከተማ በድምቀት ሲከበር ቆይቶ በሰላም ተጠናቋል። በበዓሉም ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል የመጡ የባህል ቡድኖች በጅግጅጋ ከተማ ባህላዊ ትርኢት በማቅረብ ልምድና ተሞክሯቸውን የተጋሩበትና በደስታ ያሳለፉበት ቆይታ እንደነበርም ነው የገለጹት። ዝግጅቱም ያማረና ያለአንዳች የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ለነበራቸው የፌዴራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት፣ ለጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎችና ተባባሪ አካላት ሁሉ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል። የመገናኛ ብዙኃንም በበዓሉ ላይ መታደም ያልቻሉ በአገር ውስጥና በመላው ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲደርስ ለማድረግ ላደረጉት ርብርብ ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም እንግዶች በጅግጅጋ ከተማ የነበራቸውን አስደሳች ቆይታ አጠናቀው ወደየመጡበት አካባቢ በሰላም እንዲደርሱ ሽኝት እየተደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል "ብዝኅነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች በጅግጅጋ ከተማ በድምቀት ተከብሯል። ባለፉት የኅዳር-25፣ 26፣ 27፣ 28 እና 29/2016 ዓ.ም በቅደም ተከተል "የወንድማማችነት፣ የብዝኃነት፣ የአብሮነት፣ የመደመር እና የኢትዮጵያዊነት" ቀናት በተለያዩ ደማቅ ሥነ-ስርዓቶች ተከብሮ ፍፃሜውን አግኝቷል። በዛሬው የማጠቃለያ መርሃ-ግብርም የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገርን ጨምሮ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የባህል ቡድኖች ታድመዋል።
ለአገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ድጋፋችንን እናጠናክራለን
Dec 9, 2023 45
ሶዶ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፡- ለአገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኮሚሽኑ ተባባሪ አካላት ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለተባባሪ አካላት ስልጠና መስጠቱ ይታወሳል። በዚሁ ጊዜ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጋሞ ዞን የተፎካካሪ ፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ ወንድሙ ኡቶ፣ ሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማ እንዲሆን ለኮሚሽኑ ቀጣይ ተግባራት የሚያደርጉትን ድጋፍ እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል። ምክክሩ በሀገራችን ችግሮችን በውይይት የመፍታት ባህልን የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸው ምክክሩ የህዝብ የፖለቲካና መሰል ጥያቄዎች እንደሚፈታ ያላቸውን እምነት አስረድተዋል። በምክክሩ የፓርቲ አባላትና ደጋፊዎችን በማስተባበር እንደተባባሪ አካል የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በቀጣይ ኮሚሽኑ በሚኖረው ተግባራት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች የላቀ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ሊሰራ እንደሚገባ አመልክተዋል። በክልሉ የጋርዱላ ዞን ነዋሪ ወይዘሮ ዘርትሁን ኩሴ በበኩላቸው "ተባባሪ አካል እንደመሆኔ በዚህ ረገድ ኃላፊነቴን በሚገባ እወጣለሁ" ሲሉ ተናግረዋል። ለምክክሩ ስኬታማነት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በደቡብ ኦሞ ዞን የዲመካ ከተማ ነዋሪ አቶ አርካ ዴአ በሰጡት አስተያየት "ምክክሩ መሠረታዊ በሆኑ የጋራ ጉዳዮቻችን ላይ መግባባት መፍጠርን ያለመ በመሆኑ የሚጠበቅብኝን ሃላፊነት እወጣለሁ'' ብለዋል።
አገር በቀል የሰላም ግንባታ እሴቶችን ለማጠናከር የበኩላችንን እንወጣለን
Dec 9, 2023 59
አርባ ምንጭ፤ ህዳር 29 /2016 (ኢዜአ)፡- አገር በቀል የሰላም ግንባታ እሴቶችን በማጠናከር አገራዊ ምክክሩ እንዲሳካ የድርሻቸውን እንደሚወጡ የጋሞ ዞን ምክር ቤት አባልና የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ፡፡ የተቋቋመው የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተግባር ያለመግባባት ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ እንዲፈቱና መተማመንን እንዲዳብር ለውይይት ማመቻቸት እንደሆነ ተመልክቷል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የጋሞ ዞን ምክር ቤት የሴቶችና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ዳርዛ እንደገለጹት፤ በአገሪቱ የሚስተዋሉ የተሳሳቱ ትርክቶች በህዝቡ መካከል መተማመን እንዳይኖር በማድረግ ችግር ፈጥረዋል። የችግሩ ሰለባ የሆነው ህዝብ የመፍትሄው አካል መሆን እንዳለበት ጠቅሰው፤ ምክር ቤቱ በየደረጃው የሚገኙ አባላትን በማስተባበር ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ መሳካት የበኩሉን ሚና ይወጣል ብለዋል። በየአካባቢያችን ሰላምን የምንገነባበትና ገዥ የሆነ ዕሴት አለን የሚሉት አስተያየት ሰጪው፤ እነዚህን ሀብቶች በመጠቀም አገራዊ ሰላምና አንድነት ግንባታን ለማጠናከር እያመቻቸ ላለው የምክክር ኮሚሽን ስኬታማነት የሚጠበቅብንን እንወጣለን ሲሉ ብለዋል። ከጋሞ የሀገር ሽማግሌዎች መካከል አቶ መንግስቱ ደምሴ በበኩላቸው ፤ የአገር ልማትና ብልጽግና ለማምጣት ከሁሉ በፊት አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ላይ መስራት ይገባል ብለዋል። እንደአገር በተለያዩ ምክንያቶች የተፈጠሩና ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን አሳታፊ በሆነ መልኩ የሚፈታበት ዕድል አለመፈጠሩ ችግሮቹ እየተንከባለሉ መምጣታቸውን አውስተዋል። በዚህም ስለጉዳዩ በቂ ግንዛቤና ዕውቀት እንዲሁም ግንኙነት የሌለው ትውልድ ጭምር ሰለባ እንዲሆን እንዳደረገው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ይህንን የቆየ ችግር መፍታት የሚያስችል እድል በመሆኑ ሃገር በቀል እሴቶችን በመጠቀም መፍታት እንደሚገባም ጠቅሰዋል። በጋሞ ባህልና ወግ ችግሮችን ያለምንም ቀሪ ቂምና ቁርሾ በዘላቂነት የሚፈቱበት " በዱቡሻ" የተሰኘ ባህላዊ የሸንጎ ስርዓት መኖሩን ጠቁመው፤ ይህንን ነባር ባህል ተጠቅመን አለመግባባቶችን በመፍታት ለኮሚሽኑ ስራ ስኬታማነት እንሰራለን ብለዋል። የሀሳብ ልዩነቶችን በመቻቻልና በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግሮ በመግባባት መፍታት ለሀገር በጎ ገጽታ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለውም ገልጸዋል። አቶ መንግስቱ አክለውም ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ሥራ መሳካት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ለመጪው ትውልድ ጠንካራ አንድነት ያላትና የበለጸገች አገር ማውረስ ይጠበቅብናል ብለዋል። ስልጣኔ በተስፋፋበት ዘመን ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመምከር መፍታት እንደሚገባ የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ተፈራ ኦይቻ ናቸው። የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ሥራ የህዝቡ የዘመናት ችግሮችን በመፍታት ዘላቂ ሰላምና እፎይታን የሚሰጥ ፤ ለዚህም መሰካት ሁሉም በየደረጃው ሃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ብለዋል። ለዚህም ደግሞ ሌላ አዲስ አማራጭ ሳይሆን የራሳችንን ጉዳይ በራሳችን ባህልና ወግ እንዲሁም ልምድ መሰረት በመፈተሽ ዘመናት ያስቆጠሩ ችግሮችን ጭምር በማውጣት ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እንሰራለን ነው ያሉት። አስተያየት ሰጪዎቹ እንዳመለከቱት፤አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ስራ ውጤታማ የሚሆነው ሁሉም ዜጋ የድርሻውን ሲወጣ ነው፤ በዚህ ረገድ ሁሉም ለንግግርና ሰላም ግንባታ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ በቂ ግንዛቤ መስጠት ያስፈልጋል፡፡
የብልፅግና ፓርቲ 18ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ
Dec 9, 2023 50
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2016(ኢዜአ)፦ የብልፅግና ፓርቲ 18ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፏል። ፓርቲው ያስተላለፈው የመልካም ምኞት መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፦ "ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ለ18ኛው ጊዜ በጂግጅጋ ከተማ ለሚከበረው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በአል እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን፡፡ ፓርቲያችን ብልፅግና ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በልዩ ትኩረት እየከወናቸው ከሚገኙ ጉዳዮች መካከል በቀደምት ሀገረ መንግስት ግንባታ ታሪኮቻችን ውስጥ የንትርክ እና የቁርሾ መንስኤ ሆነው በሁሉም ዘንድ ቅቡልነቱ የተረጋገጠ መንግስታዊ ስርዐት እንዳይኖረን ልዩነቶቻችንን ያሰፉ ጉዳዮችን ነቅሶ በማውጣት እልባት መስጠት ነው፡፡ በዚህ ረገድ ሀገራችን ኢትዮጵያ ብዝሀነትን እና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን አሰናስሎ በመጓዝ ዙሪያ ገጥመዋት ለነበሩ ተግዳሮቶች መፍትሄ ለመስጠት የሄድንበት ርቀት በግንባር ቀድምትነት የሚጠቀስ ጉዳይ ነው፡፡ በዘመናዊ ሀገረ መንግስት ግንባታ ታሪካችን ውስጥ እንደ ሀገር ከፈተኑን ጉዳዮች መካከል ተፈጥሯዊ የሆነውን የብዝሀነት ጥያቄን በማስተናገድ ረገድ የገጠሙን ፈተናዎች ቀላል አልነበሩም፡፡ ኢትዮጵያ ቀለመ ብዙ ሀምራዊት ሀገር መሆኗን የዘነጋው የቀደምት ሀገረ መንግስት ግንባታ ጥረታችን፤ በውስጣችን ያሉ ተፈጥሯዊ ልዩነቶች ውበት እንደሆኑ በውሉ እውቅና ያልሰጠው ፍኖተ ጉዟችን፤ ሀገራችን በበርካታ ውስብስብ ችግሮች እንድትተበተብ ብሎም በትውልድ እልፍ አእላፍ ትግሎች እና መስዋዕትነቶች ተገንብቶ የማያላቅ ውዝፍ የቤት ስራ እንድንሸከም አድርጎናል፡፡ በዘመናት መካከል ጥያቄዎች ሲነሱ፤ አብዮቶች ሲፈጠሩ ወይም የምንፈጥራቸው ስርአተ መንግስቶች ሲናጉ ሁነኛ የለውጥ እና የትግል ሀሳብ ማጠንጠኛ ሆኖ የሚነሳው ብዝሀነትን ማዕከል ያደረገው ጥያቄ ነው፡፡ ተፈጥሯዊ ማንነቴን አክብሩ፤ፍትሀዊነትን አስፍኑ፤በወል ማንነቶች ግንባታ ጉዟችሁ መለያ ማንነቴን አትርሱ የሚሉ ትግሎች ፍሬ ያፈሩ ዘንድ እንደ ሀገር የከፈልነው ዋጋ ቀላል የሚባል አልነበረም! ይህንን በውል የተደረዳው ፓርቲያችን ብልፅግና ከለውጡ በኋላ በመደመር እሳቤ የቀየሰው ሀገራዊ መንገድ በሀገራችን ውስጥ ያሉ ማንነቶች ተፈጥሯዊ መሆናቸውን እውቅና የሰጠ፤ህብረ ብሔራዊ መሆናችን ሀብት እንጂ ስጋት እንዳልሆነ የተገነዘበ፤ኢትዮጵያዊነት የጋራ ማንነታችን እንደሆነ እና ፈፅሞ ከብሔረሰባዊ ማንነታችን ጋር ሊጣረስ የማይችል እንደሆነ ባመነ ጉዞ ነው፡፡ ይህንንም በሙሉ ቁመና ማረጋገጥ እንድንችል እና ጠንካራ፤ተሻጋሪ እና ቅቡልነቱ የፀደለ ሀገረ መንግስት ግንባታ ይኖረን ዘንድ ልንላበሳቸው የሚገቡ መርሆችን እንዳሉም በወል ተገንዝበን ዴሞክራሲያዊነት እንዲያበብ፤ተቋማዊነት እንዲጠናከር፤የወንድማማችነት እና የእህትማማችነት እሳቤ እንዲፈካ የሰራናቸው በርካታ ስራዎች ውጤት ማፍራት ችለዋል፡፡ ፓርቲያችን ብልፅግና ያለ ዴሞክራሲ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን መፍጠር እንደማይቻል በአግባቡ ይረዳል፡፡ በህዝባችን ዘንድ ያሉ መሰረታዊ ጥያቄዎች ወደ አደባባይ ወጥተው ምላሽ ሊያገኙ የሚችሉት፤የፖለቲካ ነጋዴዎች የህዝብን ጥያቄ ተገን አድርገው የሚጠነስሱት እኩይ ሴራ ሊመክን የሚችለው ብሎም ቅቡልነቱ የተረጋገጠ እና ብዝሀነትን ማዕከል ያደረገ አሰባሳቢ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት መፍጠር የምንችለው ዴሞክራሲን በሙሉ ቁመና ማረጋገጥ ስንችል በመሆኑ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ሰጥተን በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን፡፡ ይህም ጥረታችን ፍሬ ያፈራ ዘንድ ከፍተኛ አስተዋፆ እያበረከተ የሚገኘው የተቋማዊነት እሳቤ ነው፡፡ሁሉም የሀገራችንን ህዝቦች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች በዘለቄታዊነት መልስ መስጠት የምንችለው፤ተፈጥሯዊ የሆነ የብዝሀነት ውቅርናችን ፍሬ የሚያፈራው፤ እንዲሁም ለሁላችንም የምትሆን ሀገር መፍጠር የምንችለው ጉዟችን በተቋማዊነት እሳቤ ሲቃኝ እንደሆነ በአግባቡ ተረድተን የወሰድናቸው እርምጃዎች አመርቂ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡ በድምሩም ወንድማማችነት እና እህትማማችነት የሚፈጥር፤በህዝቦች መሀል ያለው ትስስር የሚያጠናከር፤የአንዱ ህመም ለሌላው ህመም እንደሆነ በውል የሚገነዘብ፤ለጋራ ህልውና መረጋገጥ በጋራ መቆምን የመረጠ የፖለቲካ ስርአት መገንባት ችለናል፡፡ ውድ የሀገራችን ብሔሮች፤ብሔረሰቦች እና ህዝቦች.. ህብረ ብሔራዊ አንድነት ወደ ተሟላ የብሔራዊነት ትርክት የምንሻገርበት ድልድይ ነው! ህብረ ብሔራዊ አንድነትን መፍጠር ከቻልን መከባበር፤መቻቻል እና መተሳሰብ መርሁ ያደረገ ጠንካራ ትውልድን ማዋለድ እንችላለን፡፡ እንደ ብልፅግና ፓርቲ የምንረዳውና በሙሉ ቁመና ይረጋገጥ ዘንድ ትግል የምናደርግለት እውነታ ህብረ ብሔራዊነት ለኢትዮጵያ መፃኢ እድል የብርሀን መንገድ በመሆኑ ምክንያት ነው፡፡ በብዝሀነት ዙሪያ ለሚነሱ የውስጥ ችግሮቻችን እልባት ለመስጠት እንዲቻልም እንደ ፓርቲ የመረጥነው የመደመር እሳቤ ለችግሮቻችን በሙሉ ዘላቂ መፍትሄ እንደሚሰጥ ፈፅሞ ጥርጥር የለንም፡፡ ምክንያቱም መደመር ሀገር በቀል የሆነ እና ከእኛው ለእኛው የተቸረ እሳቤ፤ከእኛው ህመም ለእኛው የተቀመመ መድኒት በመሆኑ መሰል ችግሮችን የመፍታት አቅሙ ከፍተኛ ነው! በህዝቦች ዘንድ የተመጣጠነ ውክልና ዳግም ጥያቄ እንዳይሆን፤ቀጣዩ ትውልድ ላለፉት 50 አመታት ስንዳክርባቸው በኖሩ ጥያቄዎች ዳግም እንዳይፈተን፤ብዝሀነታችን ፈፅሞ ፈተና እንዳይሆን በእስካሁኑ ጉዟችን ያገኘናቸው ወረቶች በማካበት እንዲሁም ያጋጠሙንን ፈተናዎች በማረም ለብሔራዊነት ትርክት ግንባታ በጋራ ልንንቀሳቀስ ይገባል፡፡ የህብረ ብሔራዊነት ምሳሌ በሆነችው በጅግጅጋ ከተማ 18ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓለንም ስናከብር ይህንን አሰባሳቢ ትውልድ ተሻጋሪ ትርክት ለመገንባት ጥረት በማድረግ ሊሆን እንደሚገባ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡ ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት መረጋገጥ ያለውን ፋይዳም በውል ተገንዝበን ለአንዲት ታፍራ እና ተከብራ ለምትኖር ሉዐላዊት ሀገር ግንባታ የበኩላችንን ድርሻ እንድንወጣ አደራ ማለት እንፈልጋለን፡፡ ብልፅግና ፓርቲ ህዳር 29 2016 ዓ.ም
የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ኢትዮጵያን ለማበልጸግ የሰነቅነውን ራዕይ ዕውን ለማድረግ የገባነውን ቃል የምናድስበት ቀን ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Dec 9, 2023 54
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፦ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ኢትዮጵያን ለማበልጸግ የሰነቅነውን ታላቅ ራዕይ ዕውን ለማድረግ የገባነውን ቃል ኪዳን የምናድስበት ቀን ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። 18ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል "ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተከበረ ይገኛል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጅግጅጋ በድምቀት እየተከበረ ለሚገኘው ለ18ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የመልካም ምኞት መልዕክታቸው ይህ ዕለት በብዝሀነት ውስጥ አንድነት የሚደምቅበት፣ ሕብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ያስተሳሰረን ህዝቦች በድምቀት በጋራ የምናከብርው፣ በልዩነቶች ውስጥ ያለው አንድነት ጎልቶ የሚታይበት ነውም ብለዋል። ከንቲባዋ አክለውም በዓሉ ኢትዮጵያን ለማበልጸግ የሰነቅነውን ታላቅ ራዕይ ዕውን ለማድረግ የገባነውን ቃል ኪዳን የምናድስበት ቀን ነው ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያዊነት አንድ ዓይነትነት አይደለም፤ ኢትዮጵያዊነት መለያየትም አይደለም፤ ኢትዮጵያውያን ከሚለያዩን ጉዳዮች ይልቅ በአንድነት ያጋመዱን ጉዳዮች ይበዛሉ ሲሉም አክለዋል ከንቲባዋ። ኢትዮጵያዊነት መጠሪያችን ብቻ ሳይሆን፣ ማንነታችንም ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ መልካም በዓል ይሁንልን ሲሉም የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በሱዳን ያለው ግጭት በሰላም እንዲቋጭ የሚደረገውን ጥረት በፅኑ ትደግፋለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Dec 9, 2023 54
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ በሱዳን ያለው ግጭት በሰላም እንዲቋጭ የሚደረገውን ጥረት በፅኑ ትደግፋለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ወንድሜ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ በሱዳን ጉዳይ ላይ የተካሄደውን 41ኛውን የኢጋድ ልዩ የመሪዎች ጉባኤ በማስተናገዳቸው ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ባወጣው መረጃ ደግሞ ኢትዮጵያ በኢጋድ የሚደረገውን የሰላም እና መረጋጋት ሂደት በንቃት በመደገፍ ላይ መቆየቷ አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩና የልኡካን ቡድናቸው ተሳትፏቸውን አጠናቀው ዛሬ ማምሻውን ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸውንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያየ
Dec 9, 2023 42
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29 /2016 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአፍሪካ እና በመካለኛው ምስራቅ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር የበይነ መረብ ውይይት አደረገ ፡፡ የውይይት መድረኩ የዲያስፖራው ማህበረሰብ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ንቁ ተሳትፎና ድጋፍ እንዲያደርግ ግንዛቤን መፍጠር ያለመ መሆኑ ተመላክቷል ፡፡ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፈን አርአያ ባደረጉት የውይይቱ መክፈቻ ንግግር ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተመካክሮ መግባባት ለሀገራችን መጻኢ ተስፋ እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል ፡፡ በውይይቱ ስለ ሀገራዊ ምክክሩ መሰረታዊ ፅንሰ-ሀሳቦች ፣ በኮሚሽኑ ስለተከናወኑ አንኳር ተግባራት እና ኮሚሽኑ ስለሚገዛባቸው የህግ ማዕቀፎች ማብራርያ ተሰጥቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኮሚሽኑ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የዲያስፖራ አባላት ጋር በትብብር ስለሚሰራባቸው መንገዶች ላይ ሀሳብ እና አስተያየቶች በውይይቱ ቀርበዋል፡፡ በመጪዎቹ ጊዜያት ኮሚሽኑ መሰል ውይይቶችን በሌሎች የዓለማችን ክፍሎች ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በማድረግ ለሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን እንደሚሰበሰብ ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማህበራዊ ድኅረ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበር ህዝቦች ይበልጥ እንዲተዋወቁ ማስቻሉን የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ገለጹ
Dec 9, 2023 47
መቱ/ ነቀምቴ፤ሕዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፦ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበር ህዝቦች ይበልጥ እንዲተዋወቁ፣ አንድነትና ወንድማማችነት እንዲጠናከር እድል እየፈጠረ ነው ሲሉ የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተናገሩ። የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የዘንድሮውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ባከበሩበት ወቅት በዓሉ የሕዝቦችን ወንድማማችነት እያጠናከረ ነው ብለዋል። ተማሪ ኬን ኩዌስ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበር ዜጎች ይበልጥ እንዲተዋወቁና እንዲከባበሩ እድል ፈጥሯል ብላለች። ''ከሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች መጥተን ተከባብረንና ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን ጠብቀን እየተማርን ነው'' ያለቸው ተማሪ ኬን ''በዓሉ አንድነታችንን ለማጠናከር አግዞናል'' ስትልም ገልጻለች። ተማሪ ፈትያ መኪ ሰይድ በበኩሏ ለኢትዮጵያ ሰላምና ዕድገት እውን መሆን ለልዩነቶቻችን እውቅና የመስጠት እንዲሁም የመከባበር፣ አብሮነትን ማጎልበት ይገባል ብላለች። ለዚህ ደግሞ እንደ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን ያሉ የጋራ ጉዳዮቻችንን ማሳደግ የሚያችሉ መድረኮች ወሳኝና ይበልጥ የመተዋወቂያና መቀራረቢያ መድረኮች መሆናቸውን ተናግራለች። ዩኒቨርሲቲዎች ከተለያዩ የብሔር፣ የቋንቋ፣ የኃይማኖትና ሌሎች ብዝኃነቶች የመጡ ተማሪዎች ለዓመታት በጋራ የሚቆዩበት እንደመሆኑ ለኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት መጎልበት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የተናገረችው ደግሞ ተማሪ ሲፈን ድሪባ ናት። በተለይ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መከበሩ ትልቅ ትስስር የሚፈጥር መሆኑን ተናግራለች። የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረት ፕሬዚዳንት ተማሪ ኩምሳ ታምሩ በበኩሉ ''በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ልዩነቶቻችንን አክብረንና አንድነታችንን ጠብቀን የምናሳልፈው ጊዜ ለኢትዮጵያዊ አንድነት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው'' ብሏል። የብሔር ብሕረሰቦች ቀን መከበሩ ለእኩልነት፣ ለአንድነት፣ ለአብሮነት፣ ለትውውቅና ለወንድማማችነት መጠናከር ትልቅ ዕድልን የፈጠረ ነው ሲልም አክሏል። በተመሳሳይ የወለጋ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ የአስተዳደር ሰራተኞች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዓሉን አክብረዋል። የበዓሉ ተሳታፊ ተማሪዎች፣ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ውበታችንን የምናጎላበትና አንዱ ሌላው የሚያውቅበት ነው ብለዋል። ተማሪ ገመቺስ ታከለ፣ የሌላውን ማንነት ማክበር ራስን ማስከበር መሆኑን ገልጻ ሁሉም ተቻችሎ እና ተከባብሮ አገሩን ማሳደግ አለበት ብላለች። ተማሪ መለሰ ያእቆብ በዩኒቨርሲቲው እርስ በርስ ተከባብረው ያለችግር ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ ገልጿል። የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሀሰን ዩሱፍ፣ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበር እኩልነትና ብዝሃነት ማስተዋወቅ መሆኑን አስረድተዋል። የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብም በፍቅርና በመከባበር የተሻለ ዜጋ የማፍራቱን ስራ ማጠናከር እንዳለባቸው አሳስበዋል። በወለጋ ዩኒቨርስቲ 18ኛው የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ላለፉት አምስት ቀናት በተለያዩ ፕሮግራሞች ሲከበር መቆየቱም ታውቋል።
በጅግጅጋ ከተማ ሲከበር የነበረው 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በሰላም ተጠናቀቀ
Dec 9, 2023 70
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፡- በጅግጅጋ ከተማ በድምቀት ሲከበር የነበረው 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በሰላም መጠናቀቁን የሶማሌ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል። የሶማሌ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ ፈርሃን ጅብሪል ለኢዜአ እንደገለጹት 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ለተከታታይ ቀናት በጅግጅጋ ከተማ በድምቀት ሲከበር ቆይቶ በሰላም ተጠናቋል። በበዓሉም ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል የመጡ የባህል ቡድኖች በጅግጅጋ ከተማ ባህላዊ ትርኢት በማቅረብ ልምድና ተሞክሯቸውን የተጋሩበትና በደስታ ያሳለፉበት ቆይታ እንደነበርም ነው የገለጹት። ዝግጅቱም ያማረና ያለአንዳች የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ለነበራቸው የፌዴራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት፣ ለጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎችና ተባባሪ አካላት ሁሉ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል። የመገናኛ ብዙኃንም በበዓሉ ላይ መታደም ያልቻሉ በአገር ውስጥና በመላው ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲደርስ ለማድረግ ላደረጉት ርብርብ ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም እንግዶች በጅግጅጋ ከተማ የነበራቸውን አስደሳች ቆይታ አጠናቀው ወደየመጡበት አካባቢ በሰላም እንዲደርሱ ሽኝት እየተደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል "ብዝኅነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች በጅግጅጋ ከተማ በድምቀት ተከብሯል። ባለፉት የኅዳር-25፣ 26፣ 27፣ 28 እና 29/2016 ዓ.ም በቅደም ተከተል "የወንድማማችነት፣ የብዝኃነት፣ የአብሮነት፣ የመደመር እና የኢትዮጵያዊነት" ቀናት በተለያዩ ደማቅ ሥነ-ስርዓቶች ተከብሮ ፍፃሜውን አግኝቷል። በዛሬው የማጠቃለያ መርሃ-ግብርም የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገርን ጨምሮ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የባህል ቡድኖች ታድመዋል።
ለአገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ድጋፋችንን እናጠናክራለን
Dec 9, 2023 45
ሶዶ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፡- ለአገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኮሚሽኑ ተባባሪ አካላት ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለተባባሪ አካላት ስልጠና መስጠቱ ይታወሳል። በዚሁ ጊዜ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጋሞ ዞን የተፎካካሪ ፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ ወንድሙ ኡቶ፣ ሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማ እንዲሆን ለኮሚሽኑ ቀጣይ ተግባራት የሚያደርጉትን ድጋፍ እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል። ምክክሩ በሀገራችን ችግሮችን በውይይት የመፍታት ባህልን የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸው ምክክሩ የህዝብ የፖለቲካና መሰል ጥያቄዎች እንደሚፈታ ያላቸውን እምነት አስረድተዋል። በምክክሩ የፓርቲ አባላትና ደጋፊዎችን በማስተባበር እንደተባባሪ አካል የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በቀጣይ ኮሚሽኑ በሚኖረው ተግባራት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች የላቀ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ሊሰራ እንደሚገባ አመልክተዋል። በክልሉ የጋርዱላ ዞን ነዋሪ ወይዘሮ ዘርትሁን ኩሴ በበኩላቸው "ተባባሪ አካል እንደመሆኔ በዚህ ረገድ ኃላፊነቴን በሚገባ እወጣለሁ" ሲሉ ተናግረዋል። ለምክክሩ ስኬታማነት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በደቡብ ኦሞ ዞን የዲመካ ከተማ ነዋሪ አቶ አርካ ዴአ በሰጡት አስተያየት "ምክክሩ መሠረታዊ በሆኑ የጋራ ጉዳዮቻችን ላይ መግባባት መፍጠርን ያለመ በመሆኑ የሚጠበቅብኝን ሃላፊነት እወጣለሁ'' ብለዋል።
አገር በቀል የሰላም ግንባታ እሴቶችን ለማጠናከር የበኩላችንን እንወጣለን
Dec 9, 2023 59
አርባ ምንጭ፤ ህዳር 29 /2016 (ኢዜአ)፡- አገር በቀል የሰላም ግንባታ እሴቶችን በማጠናከር አገራዊ ምክክሩ እንዲሳካ የድርሻቸውን እንደሚወጡ የጋሞ ዞን ምክር ቤት አባልና የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ፡፡ የተቋቋመው የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተግባር ያለመግባባት ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ እንዲፈቱና መተማመንን እንዲዳብር ለውይይት ማመቻቸት እንደሆነ ተመልክቷል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የጋሞ ዞን ምክር ቤት የሴቶችና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ዳርዛ እንደገለጹት፤ በአገሪቱ የሚስተዋሉ የተሳሳቱ ትርክቶች በህዝቡ መካከል መተማመን እንዳይኖር በማድረግ ችግር ፈጥረዋል። የችግሩ ሰለባ የሆነው ህዝብ የመፍትሄው አካል መሆን እንዳለበት ጠቅሰው፤ ምክር ቤቱ በየደረጃው የሚገኙ አባላትን በማስተባበር ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ መሳካት የበኩሉን ሚና ይወጣል ብለዋል። በየአካባቢያችን ሰላምን የምንገነባበትና ገዥ የሆነ ዕሴት አለን የሚሉት አስተያየት ሰጪው፤ እነዚህን ሀብቶች በመጠቀም አገራዊ ሰላምና አንድነት ግንባታን ለማጠናከር እያመቻቸ ላለው የምክክር ኮሚሽን ስኬታማነት የሚጠበቅብንን እንወጣለን ሲሉ ብለዋል። ከጋሞ የሀገር ሽማግሌዎች መካከል አቶ መንግስቱ ደምሴ በበኩላቸው ፤ የአገር ልማትና ብልጽግና ለማምጣት ከሁሉ በፊት አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ላይ መስራት ይገባል ብለዋል። እንደአገር በተለያዩ ምክንያቶች የተፈጠሩና ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን አሳታፊ በሆነ መልኩ የሚፈታበት ዕድል አለመፈጠሩ ችግሮቹ እየተንከባለሉ መምጣታቸውን አውስተዋል። በዚህም ስለጉዳዩ በቂ ግንዛቤና ዕውቀት እንዲሁም ግንኙነት የሌለው ትውልድ ጭምር ሰለባ እንዲሆን እንዳደረገው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ይህንን የቆየ ችግር መፍታት የሚያስችል እድል በመሆኑ ሃገር በቀል እሴቶችን በመጠቀም መፍታት እንደሚገባም ጠቅሰዋል። በጋሞ ባህልና ወግ ችግሮችን ያለምንም ቀሪ ቂምና ቁርሾ በዘላቂነት የሚፈቱበት " በዱቡሻ" የተሰኘ ባህላዊ የሸንጎ ስርዓት መኖሩን ጠቁመው፤ ይህንን ነባር ባህል ተጠቅመን አለመግባባቶችን በመፍታት ለኮሚሽኑ ስራ ስኬታማነት እንሰራለን ብለዋል። የሀሳብ ልዩነቶችን በመቻቻልና በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግሮ በመግባባት መፍታት ለሀገር በጎ ገጽታ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለውም ገልጸዋል። አቶ መንግስቱ አክለውም ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ሥራ መሳካት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ለመጪው ትውልድ ጠንካራ አንድነት ያላትና የበለጸገች አገር ማውረስ ይጠበቅብናል ብለዋል። ስልጣኔ በተስፋፋበት ዘመን ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመምከር መፍታት እንደሚገባ የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ተፈራ ኦይቻ ናቸው። የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ሥራ የህዝቡ የዘመናት ችግሮችን በመፍታት ዘላቂ ሰላምና እፎይታን የሚሰጥ ፤ ለዚህም መሰካት ሁሉም በየደረጃው ሃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ብለዋል። ለዚህም ደግሞ ሌላ አዲስ አማራጭ ሳይሆን የራሳችንን ጉዳይ በራሳችን ባህልና ወግ እንዲሁም ልምድ መሰረት በመፈተሽ ዘመናት ያስቆጠሩ ችግሮችን ጭምር በማውጣት ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እንሰራለን ነው ያሉት። አስተያየት ሰጪዎቹ እንዳመለከቱት፤አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ስራ ውጤታማ የሚሆነው ሁሉም ዜጋ የድርሻውን ሲወጣ ነው፤ በዚህ ረገድ ሁሉም ለንግግርና ሰላም ግንባታ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ በቂ ግንዛቤ መስጠት ያስፈልጋል፡፡
የብልፅግና ፓርቲ 18ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ
Dec 9, 2023 50
አዲስ አበባ፤ ህዳር 29/2016(ኢዜአ)፦ የብልፅግና ፓርቲ 18ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፏል። ፓርቲው ያስተላለፈው የመልካም ምኞት መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፦ "ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ለ18ኛው ጊዜ በጂግጅጋ ከተማ ለሚከበረው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በአል እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን፡፡ ፓርቲያችን ብልፅግና ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በልዩ ትኩረት እየከወናቸው ከሚገኙ ጉዳዮች መካከል በቀደምት ሀገረ መንግስት ግንባታ ታሪኮቻችን ውስጥ የንትርክ እና የቁርሾ መንስኤ ሆነው በሁሉም ዘንድ ቅቡልነቱ የተረጋገጠ መንግስታዊ ስርዐት እንዳይኖረን ልዩነቶቻችንን ያሰፉ ጉዳዮችን ነቅሶ በማውጣት እልባት መስጠት ነው፡፡ በዚህ ረገድ ሀገራችን ኢትዮጵያ ብዝሀነትን እና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን አሰናስሎ በመጓዝ ዙሪያ ገጥመዋት ለነበሩ ተግዳሮቶች መፍትሄ ለመስጠት የሄድንበት ርቀት በግንባር ቀድምትነት የሚጠቀስ ጉዳይ ነው፡፡ በዘመናዊ ሀገረ መንግስት ግንባታ ታሪካችን ውስጥ እንደ ሀገር ከፈተኑን ጉዳዮች መካከል ተፈጥሯዊ የሆነውን የብዝሀነት ጥያቄን በማስተናገድ ረገድ የገጠሙን ፈተናዎች ቀላል አልነበሩም፡፡ ኢትዮጵያ ቀለመ ብዙ ሀምራዊት ሀገር መሆኗን የዘነጋው የቀደምት ሀገረ መንግስት ግንባታ ጥረታችን፤ በውስጣችን ያሉ ተፈጥሯዊ ልዩነቶች ውበት እንደሆኑ በውሉ እውቅና ያልሰጠው ፍኖተ ጉዟችን፤ ሀገራችን በበርካታ ውስብስብ ችግሮች እንድትተበተብ ብሎም በትውልድ እልፍ አእላፍ ትግሎች እና መስዋዕትነቶች ተገንብቶ የማያላቅ ውዝፍ የቤት ስራ እንድንሸከም አድርጎናል፡፡ በዘመናት መካከል ጥያቄዎች ሲነሱ፤ አብዮቶች ሲፈጠሩ ወይም የምንፈጥራቸው ስርአተ መንግስቶች ሲናጉ ሁነኛ የለውጥ እና የትግል ሀሳብ ማጠንጠኛ ሆኖ የሚነሳው ብዝሀነትን ማዕከል ያደረገው ጥያቄ ነው፡፡ ተፈጥሯዊ ማንነቴን አክብሩ፤ፍትሀዊነትን አስፍኑ፤በወል ማንነቶች ግንባታ ጉዟችሁ መለያ ማንነቴን አትርሱ የሚሉ ትግሎች ፍሬ ያፈሩ ዘንድ እንደ ሀገር የከፈልነው ዋጋ ቀላል የሚባል አልነበረም! ይህንን በውል የተደረዳው ፓርቲያችን ብልፅግና ከለውጡ በኋላ በመደመር እሳቤ የቀየሰው ሀገራዊ መንገድ በሀገራችን ውስጥ ያሉ ማንነቶች ተፈጥሯዊ መሆናቸውን እውቅና የሰጠ፤ህብረ ብሔራዊ መሆናችን ሀብት እንጂ ስጋት እንዳልሆነ የተገነዘበ፤ኢትዮጵያዊነት የጋራ ማንነታችን እንደሆነ እና ፈፅሞ ከብሔረሰባዊ ማንነታችን ጋር ሊጣረስ የማይችል እንደሆነ ባመነ ጉዞ ነው፡፡ ይህንንም በሙሉ ቁመና ማረጋገጥ እንድንችል እና ጠንካራ፤ተሻጋሪ እና ቅቡልነቱ የፀደለ ሀገረ መንግስት ግንባታ ይኖረን ዘንድ ልንላበሳቸው የሚገቡ መርሆችን እንዳሉም በወል ተገንዝበን ዴሞክራሲያዊነት እንዲያበብ፤ተቋማዊነት እንዲጠናከር፤የወንድማማችነት እና የእህትማማችነት እሳቤ እንዲፈካ የሰራናቸው በርካታ ስራዎች ውጤት ማፍራት ችለዋል፡፡ ፓርቲያችን ብልፅግና ያለ ዴሞክራሲ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን መፍጠር እንደማይቻል በአግባቡ ይረዳል፡፡ በህዝባችን ዘንድ ያሉ መሰረታዊ ጥያቄዎች ወደ አደባባይ ወጥተው ምላሽ ሊያገኙ የሚችሉት፤የፖለቲካ ነጋዴዎች የህዝብን ጥያቄ ተገን አድርገው የሚጠነስሱት እኩይ ሴራ ሊመክን የሚችለው ብሎም ቅቡልነቱ የተረጋገጠ እና ብዝሀነትን ማዕከል ያደረገ አሰባሳቢ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት መፍጠር የምንችለው ዴሞክራሲን በሙሉ ቁመና ማረጋገጥ ስንችል በመሆኑ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ሰጥተን በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን፡፡ ይህም ጥረታችን ፍሬ ያፈራ ዘንድ ከፍተኛ አስተዋፆ እያበረከተ የሚገኘው የተቋማዊነት እሳቤ ነው፡፡ሁሉም የሀገራችንን ህዝቦች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች በዘለቄታዊነት መልስ መስጠት የምንችለው፤ተፈጥሯዊ የሆነ የብዝሀነት ውቅርናችን ፍሬ የሚያፈራው፤ እንዲሁም ለሁላችንም የምትሆን ሀገር መፍጠር የምንችለው ጉዟችን በተቋማዊነት እሳቤ ሲቃኝ እንደሆነ በአግባቡ ተረድተን የወሰድናቸው እርምጃዎች አመርቂ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡ በድምሩም ወንድማማችነት እና እህትማማችነት የሚፈጥር፤በህዝቦች መሀል ያለው ትስስር የሚያጠናከር፤የአንዱ ህመም ለሌላው ህመም እንደሆነ በውል የሚገነዘብ፤ለጋራ ህልውና መረጋገጥ በጋራ መቆምን የመረጠ የፖለቲካ ስርአት መገንባት ችለናል፡፡ ውድ የሀገራችን ብሔሮች፤ብሔረሰቦች እና ህዝቦች.. ህብረ ብሔራዊ አንድነት ወደ ተሟላ የብሔራዊነት ትርክት የምንሻገርበት ድልድይ ነው! ህብረ ብሔራዊ አንድነትን መፍጠር ከቻልን መከባበር፤መቻቻል እና መተሳሰብ መርሁ ያደረገ ጠንካራ ትውልድን ማዋለድ እንችላለን፡፡ እንደ ብልፅግና ፓርቲ የምንረዳውና በሙሉ ቁመና ይረጋገጥ ዘንድ ትግል የምናደርግለት እውነታ ህብረ ብሔራዊነት ለኢትዮጵያ መፃኢ እድል የብርሀን መንገድ በመሆኑ ምክንያት ነው፡፡ በብዝሀነት ዙሪያ ለሚነሱ የውስጥ ችግሮቻችን እልባት ለመስጠት እንዲቻልም እንደ ፓርቲ የመረጥነው የመደመር እሳቤ ለችግሮቻችን በሙሉ ዘላቂ መፍትሄ እንደሚሰጥ ፈፅሞ ጥርጥር የለንም፡፡ ምክንያቱም መደመር ሀገር በቀል የሆነ እና ከእኛው ለእኛው የተቸረ እሳቤ፤ከእኛው ህመም ለእኛው የተቀመመ መድኒት በመሆኑ መሰል ችግሮችን የመፍታት አቅሙ ከፍተኛ ነው! በህዝቦች ዘንድ የተመጣጠነ ውክልና ዳግም ጥያቄ እንዳይሆን፤ቀጣዩ ትውልድ ላለፉት 50 አመታት ስንዳክርባቸው በኖሩ ጥያቄዎች ዳግም እንዳይፈተን፤ብዝሀነታችን ፈፅሞ ፈተና እንዳይሆን በእስካሁኑ ጉዟችን ያገኘናቸው ወረቶች በማካበት እንዲሁም ያጋጠሙንን ፈተናዎች በማረም ለብሔራዊነት ትርክት ግንባታ በጋራ ልንንቀሳቀስ ይገባል፡፡ የህብረ ብሔራዊነት ምሳሌ በሆነችው በጅግጅጋ ከተማ 18ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓለንም ስናከብር ይህንን አሰባሳቢ ትውልድ ተሻጋሪ ትርክት ለመገንባት ጥረት በማድረግ ሊሆን እንደሚገባ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡ ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት መረጋገጥ ያለውን ፋይዳም በውል ተገንዝበን ለአንዲት ታፍራ እና ተከብራ ለምትኖር ሉዐላዊት ሀገር ግንባታ የበኩላችንን ድርሻ እንድንወጣ አደራ ማለት እንፈልጋለን፡፡ ብልፅግና ፓርቲ ህዳር 29 2016 ዓ.ም
የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ኢትዮጵያን ለማበልጸግ የሰነቅነውን ራዕይ ዕውን ለማድረግ የገባነውን ቃል የምናድስበት ቀን ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Dec 9, 2023 54
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፦ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ኢትዮጵያን ለማበልጸግ የሰነቅነውን ታላቅ ራዕይ ዕውን ለማድረግ የገባነውን ቃል ኪዳን የምናድስበት ቀን ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። 18ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል "ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተከበረ ይገኛል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጅግጅጋ በድምቀት እየተከበረ ለሚገኘው ለ18ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የመልካም ምኞት መልዕክታቸው ይህ ዕለት በብዝሀነት ውስጥ አንድነት የሚደምቅበት፣ ሕብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ያስተሳሰረን ህዝቦች በድምቀት በጋራ የምናከብርው፣ በልዩነቶች ውስጥ ያለው አንድነት ጎልቶ የሚታይበት ነውም ብለዋል። ከንቲባዋ አክለውም በዓሉ ኢትዮጵያን ለማበልጸግ የሰነቅነውን ታላቅ ራዕይ ዕውን ለማድረግ የገባነውን ቃል ኪዳን የምናድስበት ቀን ነው ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያዊነት አንድ ዓይነትነት አይደለም፤ ኢትዮጵያዊነት መለያየትም አይደለም፤ ኢትዮጵያውያን ከሚለያዩን ጉዳዮች ይልቅ በአንድነት ያጋመዱን ጉዳዮች ይበዛሉ ሲሉም አክለዋል ከንቲባዋ። ኢትዮጵያዊነት መጠሪያችን ብቻ ሳይሆን፣ ማንነታችንም ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ መልካም በዓል ይሁንልን ሲሉም የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ማህበራዊ
የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ በሚያደርግልን ድጋፍ የተረጋጋ ህይወት እየመራን ነው - ስደተኞች
Dec 9, 2023 45
ጎንደር ፤ ህዳር 29 /2016 (ኢዜአ) ፡- የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ በሚያደርግልን ድጋፍ የተረጋጋ ኑሮ ለመምራት ችለናል ሲሉ በዳባት አለም ዋጭ የስደተኞች መጠለያ የሚገኙ የጎረቤት አገር ስደተኞች ተናገሩ፡፡ ስደተኞቹ የዳባትና አካባቢው ማህበረሰብ ባለፉት አራት ወራት ላደረገላቸው ሰብአዊ ድጋፍ የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ዛሬ በመጠለያው አካሂደዋል፡፡ የስደተኞች ተወካይ አቶ ሰለሞን ተስፋማርያም በስነ ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ መንግስትና የዳባት አካባቢው ህዝብ ባለፉት አራት ወራት አለም አቀፍ ረጅ ድርጅቶች እርዳታ ባቋረጡበት ወቅት ያደረጉላቸው ድጋፍና እንክብካቤ በታሪክ ሲታወስ የሚኖር ነው። የምግብ እህልና ሌሎች ሰብአዊ ድጋፎችን በመጠለያው ለሚገኙ ስደተኞች በማቅረብ የመደጋገፍና የመተሳሰብ ጥልቅ ማህበራዊ እሴታቸውን በተግባር አሳይተውናል ሲሉ ገልጸዋል። "ከአገሬ ኤርትራ ተሰድጄ ከመጣሁ ጀምሮ የአካባቢው ማህበረሰብ ከአቀባበል ጀምሮ ያደረጉልን ድጋፍ ኢትዮጵያን እንደ ሀገሬ እንድመለከት አድርጎኛል" ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ፊወሪ እቁባይ ናቸው፡፡ "ማህበረሰቡ ለስደተኞች የሚያደርገው እገዛና እንክብካቤ ፍጹም ያለስጋት የተረጋጋ ህይወት እንድንኖር አድርጎናል" ያሉት ወይዘሮ ፊወሪ፤ እርዳታ በተቋረጠበት ወቅት ለእኛንና ለልጆቻችን የተለየ ድጋፍ በማድረግ ተንከባክበውናል ብለዋል፡፡ ሌላዋ ስደተኛ ወይዘሮ ዮዲት አጽብኃ ፤ የአካባቢው ማህብረሰብ ለስደተኛው የሚያሳየው ፍቅርና መተሳሰብ ወንድማማችነትንና አብሮነትን የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል። የሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር ተወካይ አቶ አስማረ አበራ በእለቱ እንዳሉት ፤ ስደተኞቹ መብታቸው ተከብሮ ሰላማዊና የተረጋጋ ህይወት እንዲመሩ በማድረግ ረገድ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ስራ ተከናውኗል፡፡ የዞኑ አስተዳደር በዳባት ከተማ 90 ሄክታር የሚሸፍን መሬት ለስደተኛ መጠለያ ቦታ በማዘጋጀት ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ መደገፉን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም በስደተኞቹና የአካባቢው ማህብረሰብ ያለውን ግንኙነት ከመደገፍ የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች አገልግሎቶችን እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመጠለያ ጣቢያው ከ20ሺህ በላይ የጎረቤት ሀገር ስደተኞች እንደሚገኙ የገለጹት ደግሞ የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት የዳባት አለምዋጭ ስደተኛ መጠለያ አስተባባሪ አቶ ታምራት ደምሴ ናቸው፡፡ ለስደተኞቹ ይቀርብ የነበረው የምግብ እህል አቅርቦት ላለፉት አራት ወራት ተቋርጦ መቆየቱን ያስታወሱት አቶ ታምራት፤ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱ ዳግም መጀመሩን ገልጸዋል፡፡ የምግብ አህል አቅርቦቱ በተቋረጠበት ወቅት የአካባቢው ማህበረሰብ ስደተኞቹ ችግር እንዳይገጥማቸው በማሰብ ያልተቋረጠ የምግብ እህል ድጋፍ በማድረግ የጸና ፍቅሩን በተግባር ማረጋገጡን አንስተዋል፡፡ በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ የዞንና የወረዳ አመራር አባላት ፣ የአካባቢው ማህበረሰብና የስደተኞች ተወካዮች በተገኙበት በድጋፉ የነቃ ተሳትፈ ላበረከቱ ግለሰቦችና ድርጅቶች እውቅና ተሰጥቷል፡፡
የአክሱም ዩኒቨርሲቲ 1 ሺህ 692 አዲስ ተማሪዎችን ተቀበለ
Dec 9, 2023 38
መቀሌ፤ ህዳር 29/2016(ኢዜአ)፡- የአክሱም ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡለትን 1 ሺህ 692 አዲስ ተማሪዎች መቀበሉን አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙሉጌታ በሪሁ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሚያስተምራቸውን ተማሪዎች የተቀበለው ባለፉት ሁለት ቀናት ነው። ዩኒቨርሲቲው ከተቀበላቸው ተማሪዎች መካከል 635ቱ ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል ። ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎቹን ተቀብሎ የመማር ማስተማር ሥራውን ለማካሄድ የመኝታ፣የመማሪያና የመመገቢያ ክፍሎች ዝግጅት ማድረጉን አስረድተዋል። እንዲሁም የቅጥር ግቢውን ጽዳትና የጥገና ሥራዎች አከናውኗል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው ትምህርታቸውን በተለያዩ ምክንያቶች አቋርጠው የነበሩ 4 ሺህ 122 ተማሪዎች ተቀብሎ እያስተማረ መሆኑንም ዶክተር ሙሉጌታ ገልጸዋል። የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ከተቋቋመ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት መስኮች አስተምሮ ማስመረቁን መረጃዎች ያመለክታሉ። መቀሌ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡለትን ከአንድ ሺህ በላይ የተፈጥሮና የማህበረሰብ ሳይንስ ተማሪዎችን መቀበል እንደጀመረ ትናንት መዘገባችን ይታወሳል።
የኢትዮጵያ አቪየሽን ዩኒቨርሲቲ በቅድመ ምረቃ የዲግሪ መርሐ ግብር የመጀመሪያ ዙር ተማሪዎችን ሰኞ ይቀበላል
Dec 9, 2023 47
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) የኢትዮጵያ አቪየሽን ዩኒቨርሲቲ በቅድመ ምረቃ የዲግሪ መርሐ ግብር የመጀመሪያ ዙር ተማሪዎችን በመጪው ሰኞ እንደሚቀበል አስታወቀ። የኢትዮጵያ አቪየሽን ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ600 በላይ ተማሪዎችን አስመርቋል። በአብራሪነት 88 ፣ በበረራ መስተንግዶ 150፣ ማርኬቲንግ 264 እና በአውሮፕላን ጥገና 125 በድምሩ 627 ተማሪዎችን ነው ያስመረቀው። ከተመረቁት ተማሪዎች መካከል ሁለቱ ከአፍሪካ አገራት የመጡ ናቸው። የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ካሴ ይማም፤ በምርቃት ስነ-ስርአቱ ወቅት እንደተናገሩት ዩኒቨርስቲው ቀደም ሲል በአካዳሚ ደረጃ በርካታ የአቪየሽን ባለሙያዎችን ሲያሰለጥን ቆይቷል። ለአቪየሽን ዘርፉ እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ በማስፋት ከዚህ ዓመት ጀምሮ በሶስት የቅድመ ምረቃ የዲግሪ መርሃ ግብሮች ተማሪዎችን እንደሚያሰለጥን ጠቅሰዋል። በዚህም ዩኒቨርሰቲው ለመጀመሪያ ጊዜ በቅድመ ምረቃ የዲግሪ መርሐ ግብር ተማሪዎችን ሰኞ ታህሳስ 1/2016 ዓ.ም ይቀበላል ነው ያሉት። በተጨማሪም በአቪየሽን ማናጅመንት፣ በዴታ ሳይንስ በሁለተኛ የዲግሪ መርሐ ግብር ትምህርት ለመስጠት ዝግጅት መጨረሱን ተናግረዋል። አቪየሽኑ ቀደም ሲል በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሙያተኞችን ሲያሰለጥን የቆየ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከኤስያ ሀገራት፣ ከሩሲያና ሌሎች ሀገራት ሰልጣኞች እየመጡ መሆኑን ጠቁመዋል። በንድፈ ሃሳብ የተሰጠውን ትምህርት በተግባር ለማሰልጠን የተሟላ ቁሳቁስ መኖሩ አቪየሽኑን ተመራጭ እንዳደረገው ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ የሚሰጠውን ትምህርትም ውጤታማ እንዲሆን አስችሏል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው አየር መንገዱ ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎች ተጠቅሞ መንገደኞችንና የዕቃ ጭነትን የማጓጓዝ አቅሙን እየጨመረ ነው ብለዋል። ከዚህም ባለፈ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን የሚጠግንና የራሱን የሰው ሀይል በራሱ ማስተማርና ማብቃት የሚችል ግዙፍ የአቪየሽን ኩባንያ መሆኑንም ተናግረዋል። አየር መንገዱ 145 አውሮፕላኖችን በመያዝ በአለም አቀፍ ደረጃ 135 ከተሞችን መዳረሻ በማድረግ የበረራ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም ነው ያብራሩት። ከፍተኛ ሀብት ካላቸውና በቴክኖሎጂ ከዘመኑ አየር መንገዶች ጋር ተወዳድሮ በትርፋማነትና በእድገት መቀጠሉን በማንሳት። የድርጅቱ መሪዎች ራዕይና ዕውቀት፣ የሰራተኞች በታታሪነትና በቁርጠኝነት ማገልገል አየር መንገዱ አሁን ለደረሰበት የስኬት ምዕራፍ ትልቅ ሚና ማበርከቱን ጠቅሰው፤ ተመራቂ ተማሪዎች የድርጅቱን እድገት ለማስቀጠል በቁርጠኝነትና በጥንካሬ የመስራት ሃላፊነት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚው አክለውም ተመራቂዎች ለበረራ ደህንነት፣ ለደንበኞች አገልግሎት፣ ለመልካም የስራ ባህልና ራስን ማብቃት ትኩረት እንዲሰጡም ነው ያሳሰቡት። ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመራቂዎች በበኩላቸው በተማሩበት የሙያ መስክ አገራቸውንና ድርጅቱን በቁርጠኝነት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል። ከተመራቂዎች መካከል ከታንዛኒያ የመጡት አይሻ ሞሃመድና እና አዩቡ ኬዲሙንዲ በአቪየሽን ዩኒቨርስቲው ያገኙት እውቀት ህልማቸውን እውን ለማድረግ እንዳገዛቸው ተናግረዋል።
በማኅበራዊ ሚዲያ የሚተላለፉ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል እየተሰራ ነው
Dec 9, 2023 41
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፡- በማኅበራዊ ሚዲያ የሚተላለፉ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል የሚከናወኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ገለጸ። ባለሥልጣኑ በአዲስ አበባ ለሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መሐመድ እድሪስ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ባለሥልጣኑ ከሚያከናውናቸው ሥራዎች ውስጥ አንዱ የኃሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ሥርጭትን ለመከላከል የሚያስችል ግንዛቤ ማስጨበጫ ነው። አሁን ላይ የማኅበራዊ ሚዲያ መስፋፋትን ተከትሎ በአንዳንድ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሚተላለፉ የኃሰተኛ መረጃዎችና የጥላቻ ንግግሮች አብሮነትን የሚሸረሽሩ ግለሰቦችን ለተሳሳተ ውሳኔ የሚያጋልጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም እነዚህን ድርጊቶች ለመከላከል በተለይም ታዳጊ ተማሪዎች ኃሰተኛ መረጃዎችና የጥላቻ ንግግሮችን የመለየት ክህሎትን በመጨበጥ እንዳይሰራጭ በማድረግ የበኩላቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸውም ነው ያስረዱት። ባለሥልጣኑ ያዘጋጀው ሥልጠናም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ይህንን እንዲያውቁና እንዲከላከሉ ማስቻል መሆኑን ተናግረው ሥልጠናው በቀጣዮቹ ጊዜያትም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቁመዋል። ራስን ከጥላቻ በማጽዳት አብሮነቷ የጎለበተ አገር መገንባት እንደሚገባ ገልጸው በዚህ ሂደት በተለይም ወጣቱ ትውልድ ለአገር ግንባታ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት ሊሆን እንደሚገባም አመላክተዋል። ከሥልጠናው ተሳታፊዎች መካከል የቦሌ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪ መክሊት ገዛኸኝ ሥልጠናው ያለብንን ድክመቶችና የአጠቃቀም ችግሮችን እንድናውቅ አግዞናል ብላለች። ሌላኛው የዚሁ ትምህርት ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪ ጸጋዬ ድረስ በበኩሉ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሚለቀቁ መረጃዎችን እውነተኛነት እንዴት መለየት እንደሚቻል በሥልጠናው ለመመልከት መቻሉን ገልጿል። በተለይም መረጃዎች ምንጫቸውን እንዴት ማወቅ እንደሚቻል ለመገንዘብ መቻሉን ተናግሯል። መሰል ሥልጠናዎች በየጊዜው መስጠት እንዳለባቸው የገለጸችው ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ የደጅ አዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ሁለተኛና አጠቃላይ መሰናዶ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ ሃና ዘውዱ ናት። የኃሰተኛ መረጃዎች ከግለሰብ ጀምሮ እስከ አገር የሚደርስ ብዙ ጉዳት እንደሚያመጣ ገልጻ ይህንን ለመከላከል እንደምትሰራ አረጋግጣለች። ሥልጠናው በአዲስ አበባ ከሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል። ሥልጠናው በዋናነት የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ምንነት፣ የማኅበራዊ ሚዲያ ባህሪያት፣ እውነትን ማጣራት የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጓል።
ኢኮኖሚ
አርብቶ አደሩ በፋይናንስ ስርዓት ውስጥ ተካቶ ህይወቱን እንዲያሻሽል እየተደረገ ነው -የግብርና ሚኒስቴር
Dec 9, 2023 44
አርባ ምንጭ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ)፡- አርብቶ አደሩ በፋይናንስ ስርዓት ውስጥ ተካቶ ህይወቱን እንዲያሻሽል እየተደረገ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ጋር በመሆን በአደጋ ስጋት ቅነሳና አካታች የአርብቶ አደር ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮጀክት አፈጻጸም ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ መክሯል። በግብርና ሚኒስቴር የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻል ፕሮግራም ብሔራዊ አስተባባሪ አቶ ጀማል ዓሊ እንደገለጹት በአደጋ ስጋት ቅነሳና አካታች ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮጀክት የአርብቶ አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በፕሮጀክቱ አርብቶ አደሩ በድርቅ ጊዜ መኖ በመግዛት እንስሳቱን እንዲታደግ፣ በግብይት እንቅስቃሴ ከእንስሳቱ ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኝ እንዲሁም የባንክ ቁጠባና ብድር አገልግሎት ተጠቃሚ በመሆን ኑሮውን በዘላቂነት እንዲቀይር ካለፈው ዓመት ጥር ወር ጀምሮ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለአየር ንብረት ለውጥ የአርብቶ አደር አካባቢዎች በስፋት ተጋላጭ መሆናቸውን ጠቁመው በ5 ክልሎች የሚገኙ አርብቶ አደሮች የኢንሹራንስ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ለዚህም ከዓለም ባንክና ከኢትዮጵያ መንግስት 117 ሚሊየን ዶላር የተመደበ ሲሆን በቀጣይ 13 ሚሊየን የሚጠጉ አርብቶ አደሮችን በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን አቶ ጀማል ጠቁመዋል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ታረቀኝ ሀብቴ በበኩላቸው የክልሉ ሰፊ አርብቶ አደሮች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በየጊዜው ለአደጋ እየተጋለጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በክልሉ በድርቅ ለተጎዱ 11 ሺህ 168 አባወራና እማወራ አርብቶ አደሮችን ለማቋቋም ከ52 ሚሊየን ብር በላይ ጥቅም ላይ መዋሉንም አስታውስዋል፡፡ አርብቶ አደሩ ከድርቅ አደጋ በተጨማሪ የእንስሳት የግብይት ስርአቱ ባለመዘመኑ ከእንስሳት ሀብቱ ተገቢውን ጥቅም እያገኘ አለመሆኑን የተናገሩት ደግሞ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህብረት ሥራ ልማት ኤጀንሲ ሥራ አስኪያጅ አቶ ታመነ ታምርሶ ናቸው፡፡ ኢጀንሲው አርብቶ አደሩን በማደራጀትና ግንዛቤ በመፍጠር የባንክ ቁጠባና ብድር አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆንና በግብይት ስርአቱ ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኝ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በምክክር መድረኩ ላይ ከግብርና ሚኒስቴር፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ኮሚሽን፣ ህብረት ሥራ ልማት ኤጀንሲ፣ ከሴቶችና ህፃናት፣ ከፋይናንስ፣ ከመንገድ ልማት ቢሮና ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ ነው
Dec 9, 2023 42
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፦በኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ እና ዘርፉን ለማሳደግ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ። የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ውስጥ ያሉትን ችግሮች ለመፍታትና ዘርፉን የበለጠ ለማነቃቃት ትኩረት አድርጎ ያዘጋጀው ፎረም አዲስ አበባ ተካሂዷል። በፎረሙ ላይ የዘርፉ የፌደራልና የክልሉ የሥራ ሃላፊዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መስፍን ነገዎ፤ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የግንባታ ጥራት መጓደል፣ የግብዓት እጥረት፣ የግንባታዎች በወቅቱ ያለመጠናቀቅ፣ የግብዓት የዋጋ ንረትና ሌሎችም ችግሮች መኖራቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም መንግሥት ዘርፉን ለማሳደግ ከፖሊሲ ጀምሮ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ ነው ብለዋል። የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ናትናኤል ጌታሁን በበኩላቸው፤ በክልሉ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪን ዕድገት ለማፋጠን ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። የክልሉ መንግሥት በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶችን በመደገፍ፣ በቴክኖሎጂ እና በፈጠራ ስራዎች በመታገዝ ችግሮችን ለመቅረፍ እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የግዥ ስርዓትን በማዘመን፣ ግልጽነትን በማስፈን ጥራት ያለው መሰረት ልማት እንዲኖር ጥብቅ ክትትል ማድረግም ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው ነው ብለዋል። በኮንስትራክሽን መስኮች ላይ ከተሰማሩ ባለሃብቶች መካከል አቶ አብዲሳ እሸቱ ከግንደበረት ኮንስትራክሽን ፣አቶ ተስፋሁን ኢሳያስ ከቪክቶር ዶርስና አቶ ዮናስ ሙሉጌታ ከዮት ኮንስትራክሽን በሰጡት አስተያየት፤ ዘርፉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እድገት እያሳየ ቢመጣም አሁን ብዙ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። በግብዓት ላይ የሚስተዋል ገበያ ዋጋ አለመረጋጋት፣ የግብዓት እጥረት እና ሌሎችም ችግሮች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ መንግስት ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል። የዘርፉን ችግር ለመቅረፍ ለመንግስት ብቻ የሚሰጥ ስራ እንዳልሆነ ያነሱት አስተያየት ሰጪዎቹ ሁሉም ባለሃብት የድርሻውን መወጣት እንዳለበት ገልጸዋል።
አሲዳማ አፈርን በኖራ አክመን በማልማት ውጤታማ አድርጎናል
Dec 9, 2023 52
ጂንካ፤ ህዳር 29 /2016 (ኢዜአ) ፡- አሲዳማ አፈርን በኖራ በማከም ማልማት መቻላቸው ውጤታማ እንዳደረጋቸው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰሜን አሪ ወረዳ አስተያየታቸውን የሰጡ አርሶ አደሮች ተናገሩ። በወረዳው ጋሲና-ዘማ፣ አይካ ሰልሚ፣ ዞፍና ዳዋና ሻማ ቡልቄት ቀበሌዎች በ45 አርሶ አደር ማሳ ላይ በአሲዳማ አፈር ላይ በሙሉ ፓኬጅ በሙከራ ደረጃ የለማ የገብስና የስንዴ ማሳ ተጎብኝቷል። የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል የሰብል ተመራማሪዎች ባለፉት አራት ወራት በወረዳው አራት ቀበሌዎች በሙከራ ደረጃ የስንዴና የገብስ ምርጥ ዘርን ከኖራና፣ ከአፈር ማዳበሪያ ጋር በማዋሀድ በኩታ ገጠም በ10 ሄክታር ላይ የማላመድ ስራ ማከናወናቸው ተመልክቷል። በምርምር ሂደቱ ኖራን ከአፈር ማዳበሪያ ጋር በማዋሀድ የተዘራው ሰብል መሬቱ ያለውን አሲዳማነት በመቋቋም ከአካባቢው የሰብል ዝርያዎች በእጥፍ ምርት መስጠቱ ተረጋግጧል። በወረዳው በጋሲና ዘማ ቀበሌ በተደረገው ምልከታ በስንዴና በገብስ ልማቱ የተሳተፉ አርሶ አደሮች ውስጥ ጋስካ ክፍሌ በሰጡት አስተያየት አሲዳማ አፈርን በኖራ በማከም በሙከራ ደረጃ ማልማት የጀመርነው የሰብል ልማት ውጤታማ አድርጎናል ብለዋል። የእርሻ ማሳቸው አፈር አሲዳማ በመሆኑ ለሰብል ስለማያመች የልማት ስራቸውን አስቸጋሪ አድርጎባቸው እንደቆየ ተናግረዋል። የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከልና የግብርና ባለሙያዎች አሲዳማ አፈሩን በኖራ በማከም ስንዴና ገብስ ማልማት እንደምንችል ሲነግሩን ለማመን ተቸግረን ነበር ያሉት አርሶ አደሩ፤ባለሙያዎቹ በተግባር ሲያሳዩን በጣም ተደንቀናል ሲሉ ገልጸዋል። አርሶ አደር ኤፍሬም ጥጋቤ "በማሳችን አሲዳማ አፈሩን በኖራ በማከም በሙከራ ደረጃ ያለማነው የገብስና የሰንዴ ሰብል ከዚህ ቀደም ከምናለማቸው ሰብሎች አሲዳማነቱን በመቋቋም በእጥፍ ምርት አግኝተናል" ብለዋል። የግብርና ባለሙያዎችን ምክረ ሀሳብ ተግባራዊ ማድረጋችን ውጤታማ አድርጎናል ያሉት አርሶ አደሩ፤ ከዚህም ያገኙትን ዕውቀት በመጠቀም በቀጣይ በስፋት በማልማት ኑሮአቸውን ለመለወጥ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በመስክ ምልከታው ላይ የተሳተፉት አርሶ አደር ፅንገና ጋራ በበኩላቸው፤ ያዩትን ልምድና ተሞክሮ ወደ አካባቢያቸው በማስፋት ለማልማት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ዶክተር ተክሌ ዮሴፍ፤ ማዕከሉ በጥናትና ምርምር በማስደገፍ በአካባቢዊ ያለውን የሰብል፣ የ"ሆርቲካልቸር" እና የእንስሳት ሀብት ምርታማነት በማሳደግ የአርሶና አርብቶ አደሮችን ኑሮ ለመለወጥ እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ማዕከሉ ላለፉት አራት ወራት በሰሜን አሪ ወረዳ ሁለት ክላስተሮች አሲዳማ አፈሩን በኖራ በማከም በ45 አርሶ አደሮች ማሳ በ10 ሄክታር ላይ ስንዴና ገብስን በኩታ ገጠም ሲያለማ መቆየቱን አውስተዋል። "በሙከራ ሂደቱ የአበረታች ውጤት መገኘቱን አመልክተው፤ ከዚህ ቀደም ምንም ምርት የማይሰጡ መሬቶች ምርት መስጠት ጀምረዋል" ብለዋል። የአካባቢው አርሶ አደሮች ከዚህ ቀደም ግፋ ቢል ከአንድ ሄክታር ሁለትና ሶስት ኩንታል ምርት ያገኙ እንደነበር ጠቅሰው፤ በምርምር ማዕከሉ የምርምር ስራ እስከ 50 ኩንታል ምርት ማግኘት እንደሚቻል መረጋገጡን ተናግረዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲቱዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ያሲን ጎኣ በበኩላቸው፤ በምርምር ማዕከሉ የተገኙት ውጤቶች የተጀመረውን የስንዴ ልማት የማስፋፋት ስራን የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል። "በእጃችን ያሉ የተፈጥሮ ፀጋዎች አሟጠን በማልማት የአርሶና አርብቶ አደሮችን ህይወት ለመለወጥ በቁርጠኝነት በመስራት ሁሉም መሬቶች መልማት አለባቸው" ብለዋል። የግብርና ምርምር ማዕከላት በሰብል፣ በ"ሆርቲካልቸር" እና በእንስሳት ሀብት ምርታማነትን በእጥፍ የሚያሳድጉ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ፣ በማላመድና በማስፋፋት የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የጀመሩትን ስራ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም አሳስበዋል። በምርምር የተገኙ ውጤቶችን በማስፋት የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል እንሰራለን ያሉት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ ናቸው። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኘው መሬት በአሲዳማነት የተጠቃ መሆኑን አንስተው፤ ኖራ በስፋት በማቅረብ አፈርን እያከሙ ለማልማት መታቀዱን አንስተዋል። በጉብኝቱ ከተለያዩ አካባቢዎች የተወጣጡ አርሶ አደሮች፣ የክልልና የዞን የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል።
የመንግሥት ተቋማት የአገር ውስጥ ምርት እንዲጠቀሙ የሚያደርግ አቅጣጫ ተቀምጦ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ ነው
Dec 9, 2023 46
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016 (ኢዜአ) ፡- የመንግሥት ተቋማት የአገር ውስጥ ምርት እንዲጠቀሙ የሚያደርግ አቅጣጫ ተቀምጦ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለጹ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢንዱስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአዲስ አበባና አካባቢዋ በሚገኙ የግልና የማኅበራት አምራች ኢንዱስትሪዎች የመስክ ምልከታ አድርጓል። በዚህም የቡልኮ ጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማኅበር፣ የአዋሽ ቆዳ ፋብሪካ፣ የፎንተኒና ቆዳ ፋብሪካ፣ የአዳል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል የወረቀት ፋብሪካና የኢትዮጵያ ልህቀት ማዕከል ተጎብኝተዋል። ከመስክ ምልከታው በኋላ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እንደገለጹት፤ የአምራች ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማሳደግ "ኢትዮጵያ ታምርት" የሚል ሰፊ እንቅስቃሴ ሲደረግ መቆየቱን አውስተዋል። "በኢትዮጵያ ታምርት" እንቅስቃሴ ምርት በስፋት እንዲመረት ከማድረግ ባሻገር በተለያዩ ምክንያቶች ሥራ አቁመው የነበሩ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲመለሱ ማድረግ መቻሉን ነው የገለጹት። በማምረት አቅማቸው ዝቅ ብለው የነበሩትን ደግሞ የመደገፍ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። አሁን ደግሞ የአገር ውስጥ ምርትን በአገር ውስጥ የመጠቀም ባህልን ለማሳደግና ዘርፉን በማጠናከር አገሪቱ ከመስኩ ያላትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። ይህንንም ተከትሎ በተለይም የመንግሥት ተቋማት የአገር ውስጥ ምርትን እንዲጠቀሙ አቅጣጫ መቀመጡን ነው ያስረዱት። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢንዱስትሪና የማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር አማረች ባካሎ በበኩላቸው የመስክ ምልከታው በሪፖርት የቀረበልንን መሬት ላይ መኖሩን እንድናረጋግጥ አስችሎናል ብለዋል። ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጡ ተግባራት እያከናወነ መሆኑንም መመልከታቸውን ጠቁመው በቀጣይም እነዚህ ተግባራት መጠናከር አለባቸው ነው ያሉት። ቋሚ ኮሚቴው ለዘርፉ ተዋናዮች ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩ የሕግ ማዕቀፎች እንዲኖሩ ይሰራል ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢትዮ-ቴሌኮም ከኦሮሚያ ክልል ጋር ዲጂታል መሠረተ ልማትን ማቅረብ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ
Dec 8, 2023 67
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 28/2016 (ኢዜአ)፦ ኢትዮ-ቴሌኮም ከኦሮሚያ ክልል ጋር የአገልግሎት አሰጣጥን የሚያዘምኑና የስማርት ሲቲ ትግበራን እውን የሚያደርጉ ዲጂታል መሠረተ ልማቶችን ማቅረብ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ። ስምምነቱን የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፤ በምክትል ፕሬዚደንት ማዕረግ የኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ መስከረም ደበበና የሸገር ከተማ ከንቲባ ዶክተር ተሾመ አዱኛ ፈርመውታል። የኦሮሚያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ መስከረም ደበበ በዚህ ወቅት ክልሉ የማህበራዊና ተቋማዊ አገልግሎቶችን በስፋት የሚሰጥ እንደሆነ ገልጸዋል። በተለይም የትምህርት፣ የጤና፣ የቱሪዝምና መሠል አገልግሎቶች ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እየተሠራ ይገኛል። ለዚህም ዘመኑ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ አሰራሮችን በማስረጽ ምርትና ምርታማነትን ማጎልበት ዋነኛው ጉዳይ እንደሆነም አብራርተዋል። ስምምነቱ በዋናነት በክልሉ ያሉ ዞኖችን፣ ወረዳዎችንና ከተሞችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስተሳሰር የሚፈለገው የእድገት ደረጃ ላይ ለመድረስ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል። በዋናነት የንግድ ስርዓቱን ማዘመን የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን ማስፋት ላይም እንዲሁ የተደረገው ስምምነት ወሳኝ ስለመሆኑ አስረድተዋል። ስምምነቱ የመንግስትን የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ለማጎልበትና ከማህበረሰቡ ለሚነሱ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ ነው ተብሎ ታምኖበታል። የሸገር ከተማ ከንቲባ ዶክተር ተሾመ አዱኛ በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተሞችን የማዘመን ስራ እየተለመደ መጥቷል። የሸገር ከተማ ምስረታ ይህንኑ ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር የተደረገው ስምምነት ከተማዋን ይበልጥ ለማዘመን ይረዳል ብለዋል። በተለይም በቴክኖሎጂ የበለጸገች፣ ተስማሚና አምራች ከተማን ለመፍጠር የስምምነቱ ሚና ጉልህ እንደሚሆንም አንስተዋል። ተቋሙ የቴሌኮም መሰረተ ልማቶችን ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ የተቋማትን የዲጂታል አገልግሎቶች ማስፋት ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ናቸው። ይህም ለዲጂታል ኢትዮጵያ እውን መሆን ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ነው ያሉት። ዛሬ የተፈረሙት ስምምነቶች በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን በማፋጠን ዘመናዊነትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። በዋናነት ዲጂታላይዝ ተቋማትን መፍጠር፣ የትምህርት ተደራሽነት፣ የማዕድን ሃብት ልየታና ምርት ማዘመን እንዲሁም የግብርና ስራን በቴክኖሎጂ መደገፍ ዋነኞቹ ናቸው። በተጨማሪም የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎቶች፣ የጤና፣ የመሬት አስተዳደርና የስማርት ሲቲ ግንባታንም እንዲሁ በቴክኖሎጂ ማዘመን የስምምነቱ አካል ስለመሆኑ አስረድተዋል። ስምምነቱ የክልሉን ሃብት በተገቢው ጥቅም ላይ ለማዋል በእጅጉ የሚያግዝና የዜጎችን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ የሚያቃልል መሆኑን ጠቁመዋል። ስራውን በሚፈለገው መልኩ ለማከናወን ኢትዮ-ቴሌኮም በቁርጠኝነት እንደሚሰራም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አረጋግጠዋል።
የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ ዘርፈ-ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ ነው
Dec 7, 2023 72
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 27/2016 (ኢዜአ)፦ የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ ዘርፈ-ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ፍሬህይወት ትልቁ ገለጹ። የኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካት አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በተለይም የአገልግሎት አሰጣጥና የኢኮኖሚ ልማትን ማሳለጥ ያስፈልጋል። በመሆኑም “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂን እውን ለማድረግ በተለይም የዲጂታል ክፍያ ሥርዓትን በመዘርጋትና የዲጂታል አገልግሎትን የማስፋት ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል። ከዚህ አንጻር የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን በማስመልከት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ፍሬህይወት ትልቁ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ዋና ዳይሬክተሯ በማብራሪያቸው ተቋሙ ለመንግሥት ሠራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ዘርፈ-ብዙ የሕዝብ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ መሆኑን ገልፀዋል። የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ዲጂታል አሠራርን በማስፋት የአደጋ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችል የትራንስፖርት፣ የተሽከርካሪ ሰሌዳ፣ የመንጃ ፈቃድና ሌሎችም ቀልጣፋና የተሳለጡ አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። የተሽከርካሪ ሰሌዳ ህትመትን እያከናወነ ለሚመለከታቸው አካላት ተደራሽ የማድረግ ስራ እየተሰራም መሆኑን ጠቁመዋል። በ2016 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት በነበረው አፈጻጸም ለ60ሺህ ተሽከርካሪዎች ሰሌዳ አትሞ ማሠራጨቱን ዋና ዳይሬክተሯ ገልፀዋል። የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰለሞን አምባቸው፤ ተቋሙ በተለይም ከመንጃ ፈቃድ አሰጣጥ ጋር የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማስቀረት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር መዘርጋቱን ተናግረዋል። በዚህና በሌሎችም አገልግሎቶች ተቋሙ በአዳዲስ አሠራሮች በመታገዝ ግዴታውን በመወጣት የዲጂታል አሠራርን በስፋት ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። በ2025 ዓ.ም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በመንግሥት ሰፊ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑ ይታወቃል።
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
Dec 7, 2023 70
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 27/2016(ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በሲስተም ዝርጋታ፣ በሰው ኃይል ስልጠና እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ አብሮ መስራት የሚያስችላቸው መሆኑም ከኢንስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በዚህም የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ለዜጎች የሚሰጠውን አገልግሎት በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እገዛ ለማድረግ እንደሚያስችለው ተጠቅሷል፡፡ የመግባቢያ ሰነዱን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ኢንጅነር) እና የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ተፈራርመዋል፡፡ በሥነ-ስርዓቱ ላይ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ኢንጅነር) ባስተላለፉት መልዕክት ተቋሙ ለዜጎች የሚሰጠዉን ዘርፈ ብዙ አገልግሎት በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ ኢንስቲትዩቱ አስፈላጊዉን እገዛ ለማድረግ ቁርጠኛ ነው ብለዋል፡፡ የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በበኩላቸው ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት መስማማታቸው ተቋማቸው የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን እንደሚረዳ ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ የንብረት አስተዳደርና አጠቃቀም በዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራር ለመተግበር የሚያግዝ ሶፍትዌር ወደ ስራ ገብቷል
Dec 7, 2023 83
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 27/2016 (ኢዜአ) ፡- በአዲስ አበባ የመንግስት እና የህዝብ የንብረት አስተዳደርና አጠቃቀም በዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራር መተግበር የሚያስችል ሶፍትዌር ተመርቆ ወደ ሙሉ ትግበራ መገባቱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት ሶፍትዌሩ የመንግስትና የህዝብ ሃብትን በስርዓት ለማስተዳደር፣ ብክነትን እና ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት እንዲሁም ህንፃዎችን በመመዝገብ በትክክል አውቆ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። ሶፍትዌሩ በ20 የመንግስት ተቋማት ላይ ተሞክሮ ውጤታማነቱ የተረጋገጠ ሲሆን በተቀሩት የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ብለዋል። የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣንና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሴፍትዌሩን በትብብር ማልማታቸውን ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል።
ስፖርት
የአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ ውድድር በትንሿ ስቴድየም ተጀመረ
Dec 9, 2023 39
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ ውድድር በትንሿ ስቴድየም በዛሬው ዕለት ተጀምሯል። በአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ( ቮሊቦል) ፌዴሬሽን አማካኝነት በተዘጋጀው በዚህ ውድድር በወንዶች አምስት ክለቦች በሴቶች አራት ክለቦች የሚሳተፉበት ሲሆን እስከ ታህሳስ 14 ቀን 2016 ዓ.ም ይቆያል። በውድድሩ ማስጀመሪያ በወንዶች መቻል ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር ተጫውተው አዲስ አበባ ፖሊስ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል። በሴቶች ፌደራል ማረሚያ ቤት አዲስ ከተማን 3 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል። የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳዊት ትርፉ ተወዳጅ የሆነውን የመረብ ኳስ ስፖርት ለማስፋፋት ቢሮው በቀጣይም ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል። ዛሬ የተጀመረው ውድድር አዲስ አበባን ወክለው በሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ መድረክ ላይ የሚሳተፉ ስፖርተኞችን ለማፍራት እንደሚያስችል ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ በላይነህ ተካ በበኩላቸው የክለቦች የመረብ ኳስ ውድድር ለረዥም ጊዜ ሳይካሄድ ቆይቶ እንደነበር አስታውሰዋል። የውድድሩ ቀጣይነትም በከተማ ደረጃ የመረብ ኳስ ስፖርት እንዲያድግ እና ለፕሪሚየር ሊግ አቅም የሚሆኑ ልጆችን ለማግኘት ስፖርቱ ሊጠናከር ይገባል ብለዋል። በመረብ ኳስ (ሲቲካፕ) ውድድሩ በሴቶች ጌታ ዘሩ፣ ፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን፣ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማና ብሔራዊ አልኮል ይወዳደራሉ። በወንዶች ደግሞ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ አቃቂ ክፍለ ከተማ፣ ብሔራዊ አልኮል፣ መቻል እና አዲስ አበባ ፖሊስ በውድድሩ እንደሚካፈሉ የአዲስ አበባ ከተማ የመረብ ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል።
አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዓለም አትሌቲክስ ኢንተርናሽናል ፌርፕሌይ ሽልማትን አሸነፈች
Dec 9, 2023 44
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 29/2016(ኢዜአ) ፡- ኢትዮጵያዊቷ የረጅም ርቀት አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዓለም አትሌቲክስ ኢንተርናሽናል የስፖርታዊ ጨዋነት ሽልማት አሸናፊ መሆኗ ይፋ ተደርጓል። የአለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የአለም ፌር ፕለይ ኮሚቴ በጋራ ባደረጉት የመጨረሻ ምርጫ አትሌት ለተሰንበት ግደይ አሸናፊ መሆን ችላለች ። አትሌቷ በቡዳፔስቱ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 10 ሺህ ሜትር ሴቶች ውድድር ላይ የውድድሩ መጨረሻ ላይ ትራክ ላይ ወደ ወደቀችው ኔዘርላንዳዊት አትሌት ሲፋን አሰን በመሄድ ያሳየችው ስፖርታዊ ጨዋነት በኮሚቴው እና በተመልካቾች ምርጫ እንድታሸንፍ ማስቻሉን በመረጃው ተመልክቷል። አትሌት ለተሰንበት ግደይ ከሽልማቱ በኋላ በሰጠችው አስተያየት፤ " አትሌት ሲፋን ሀሰን ስትወድቅ ከልቤ አዝኜ ነበር ምክንያቱም ስሜቱን አውቀዋለሁ ብላለች፡፡ የ2023 የስፖርታዊ ጨዋነት ሽልማት በማሸነፌ ተደስቻለሁ ማለቷን ከአለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተገኘው መረጃ ያሳያል።
የአማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር ለስፖርት ማጠናከሪያ የሚውል ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ
Dec 8, 2023 56
ባህር ዳር፤ ህዳር 28/2016 (ኢዜአ) ፦ የአማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር ለስፖርት እንቅስቃሴ ማጠናከሪያ ድጋፍ የሚውል ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የውል ስምምነት ከባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ስፖርት መምሪያ ጋር ተፈራረመ። በአማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር የሰሜን ቀጠና ጽህፈት ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ እሸቴ የማታ ዛሬ በተካሄደው የፊርማ ስነ-ስርዓት ወቅት እንዳሉት፤ባንኩ ከሚሰጠው የባንክ አገልግሎት ባሻገር ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው። ባንኩ ባለፈው ዓመት የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብን ለማጠናከርና ‘‘አማራ ባንክ ጣና ዋንጫ’’ በሚል በባህር ዳር ለተካሄደው የቤትኪንግ ፕሪሜርሊግ የእግር ኳስ ውድድር 8 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታውሰዋል። ዛሬ የተፈራረሙት የውል ስምምነት ደግሞ ባንኩ በባህር ዳር ከተማ በሶስት ቦታዎች ለሚካሄድ ነፃ የማህበረሰብ አቀፍ የጤናና የአካል ብቃት ስፖርት እንቅስቃሴ ስልጠና የሚውል የ540 ሺህ ብር ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል። በቀጣይም ጤንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብ ለመፍጠር በጎንደር፣ በደሴና ደብረማርቆስ ከተሞች ለሚካሄድ ነፃ የማህበረሰብ አቀፍ የጤናና የአካልብቃት እንቅስቃሴ ድጋፉን እንደሚያጠናክር አስታውቀዋል። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አብርሃም አሰፋ በበኩላቸው፤ ባንኩ ዛሬ ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ የማህበረሰብ አቀፍ ስፖርት እንቅስቃሴ እንዲነቃቃና ህብረተሰቡ ጤንነቱን እንዲጠብቅ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። ባንኩ ባለፈው ዓመት በባህር ዳር ከተማ ለተካሄደ የቤትኪንግ ፒሪሜርሊግ ተሳታፊ የእግር ኳስ ውድድር ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣቱን አውስተዋል። ዛሬ የተደረገው ድጋፍ ለአንድ ዓመት ነፃ የማህበረሰብ አቀፍ የጤናና የአካል ብቃት ለሚሰጡ አሰልጣኞች የላብ መተኪያ እንደሚውል ተመልክቷ በዚህም በሳምንት ሶስት ቀን በከተማዋ በባለእግዚአብሄር፣ አዝዋና አባይ ማዶ ከጥዋቱ 12 ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት በሚካሄደው ነፃ የማህበረሰብ አቀፍ የጤናና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተጠቅሷል። ይህም ባህር ዳርን የስፖርት ቱሪዝም ከተማ ለማድረግ የተያዘውን ግብ ለማሳካትና ጤንነቱ የተጠበቀ አምራች ህብረተሰብ ለመፍጠር እየተደረገ ላለው ጥረት ፋይዳው የጎላ እንደሆነ አብራርተዋል። የአማራ ባንክ በስፖርቱ ዘርፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እያደረገ ያለውን ድጋፍም ሌሎች ባንኮች ተግባሩን በአርዓያነት ወስደው እንዲደግፉ አቶ አብርሃም ጥሪ አቅርበዋል።
የፕሪሚየር ሊጉ ሰባተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ
Dec 7, 2023 77
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 27/2016 (ኢዜአ) ፡-የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጀመራል። ወልቂጤ ከተማ ከሀምበሪቾ ዱራሜ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። በ 5 ነጥብ በሊጉ 13ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ወልቂጤ ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በሁለቱ ሲሸነፍ በሁለቱ አቻ ተለያይቷል። በ2 ነጥብ 15ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው ሀምበሪቾ ዱራሜ በሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች በሶስቱ ሲሸነፍ በሁለቱ አቻ ወጥቷል። ሀምበሪቾ ዱራሜ በሊጉ እስከ አሁን ምንም ጨዋታ አላሻነፈም። ከምሽቱ 12 ሰዓት ፋሲል ከነማ ከወላይታ ድቻ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በ12 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ፋሲል ከነማ በሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች በሶስቱ ሲያሸንፍ በሁለቱ ነጥብ ተጋርቷል። ተጋጣሚው ወላይታ ድቻ በበኩሉ ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በሁለቱ ሲሸነፍ በሁለቱ አቻ ወጥቷል። ወላይታ ድቻ በ8 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። የፕሪሚየር ሊጉ የሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ነገም ቀጥሎ ሲውል መቻል ከአዳማ ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት፤ ባህር ዳር ከተማ ከሃዋሳ ከተማ ምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። የሊጉ የሰባተኛ ሳምንት ጨዋታዎች እስከ ሕዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ይቆያሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በቆሻሻ አያያዝ፣ አጓጓዝና አወጋገድ ዙሪያ የሚታዩ ችግሮች በአፋጣኝ ሊስተካከሉ ይገባል- ቋሚ ኮሚቴው
Dec 7, 2023 70
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 27/2016 (ኢዜአ) ፡- በቆሻሻ አያያዝ፣ አጓጓዝና አወጋገድ ዙሪያ የሚታዩ ችግሮች በአፋጣኝ እንዲስተካከሉ የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣንን የ2014/2015 በጀት ዓመት የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ገምግሟል። የሁለቱን በጀት ዓመት የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ግኝት የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ለቋሚ ኮሚቴው በዝርዝር አቅርበዋል። በማብራሪያቸውም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በተለይ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝ፣ አጓጓዝ፣ አወጋገድ እና በፕላስቲክ ምርቶች ፈቃድ አሰጣጥ ላይ ጉድለቶች እንዳሉበት አመላክተዋል። ከጉድለቶቹ መካከል በገንዳዎች ላይ የሚጠራቀሙ ቆሻሻዎች ሳይነሱ ለረዥም ጊዜ እየተቀመጡ በየአካባቢው የንጽህና መጓደል እያስከተሉና የጤና እክልም እየፈጠሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። የቆሻሻ አወጋገድና የሚያስከትለውን ጉዳት በሚመለከት ለኅብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ክፍተትም መኖሩን አንስተዋል። የአሠራር ሥርዓት በማበጀት ቆሻሻን ወደ ሃብትነት የመቀየር ሥራም በሚፈለገው ልክ እየተከናወነ ባለመሆኑ እንደ ጉድለት ጠቅሰዋል። ለደረቅ ቆሻሻ አያያዝ አዋጅ ቁጥር 513/1999 እስካሁን ድረስ ደንብና መመሪያ አለማዘጋጀቱም እንዲሁ። የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ፤ በአሥር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ በ1 ሺህ 960 ከተሞች ላይ የተቀናጀ የቆሻሻ አያያዝ ሥርዓት ለመዘርጋት ታልሞ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በዚህም መሠረት እስካሁን በ249 ከተሞች ላይ ተግባራዊ መደረጉን ጠቅሰው፤ በባህር ዳር፣ ደብረ ብርሃን፣ ሰበታ እና ሻሸመኔ ከተሞች ዘመናዊ የቆሻሻ ማስወገጃ ለመገንባት ሥራ ተጀምሯል ብለዋል። በሌሎች አሥር ከተሞችም ተመሳሳይ ግንባታዎችን ለማከናወን ጥናቱ ተጠናቆ ወደ ሥራ ለመግባት ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል። ከክዋኔ ኦዲት ሪፖርቱ ለተመላከቱ ጉድለቶች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያም፤ ጉድለቶቹ የተፈጠሩት በበጀት እጥረትና በሰው ኃይል አለመሟላት መሆኑን ተናግረዋል። በሥራ ላይ ያለው አዋጅ ቁጥር 513/1999 አሁን ላይ ወቅቱን የሚመጥን ባለመሆኑ በ2012 ዓ.ም አዲስ ረቂቅ አዋጅ የተዘጋጀ ቢሆንም ፀድቆ ወደ ሥራ ባለመግባቱ በተቋሙ አሠራር ላይ ችግር ስለመፍጠሩ አንስተዋል። በቀጣይ አዋጁ ፀድቆ ወደ ሥራ እንዲገባ የመከታተልና ሌሎችም በጉድለት የተነሱ ችግሮችን ለማስተካከል እንሰራለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አራሬ ሞሲሳ፤ በቆሻሻ አያያዝ፣ አጓጓዝና አወጋገድ ዙሪያ የሚታዩ ችግሮች በአፋጣኝ ሊስተካከሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። በመሆኑም የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ፣ አጓጓዝ፣ አወጋገድ እና የፕላስቲክ ምርቶች ፈቃድ አሰጣጥ አዋጅ ፀድቆ በአጭር ጊዜ መመሪያ ተዘጋጅቶለት ወደ ሥራ እንዲገባ ባለሥልጣኑ የሚጠበቅበትን ሊሰራ ይገባል ብለዋል። የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱን ጥረቶች በማገዝና በመደገፍ ረገድ ቋሚ ኮሚቴው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲሁም ክትትል ያደርጋል ብለዋል።
አየር ጠባይ ለውጥ ምክንያት የሚያጋጥሙ የተለያዩ አደጋዎችን ለመቀነስ ኢትዮጵያ በትኩረት እየሰራች ነው
Dec 4, 2023 123
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 24/2016 (ኢዜአ) ፡- በአየር ጠባይ ለውጥ ምክንያት የሚያጋጥሙ የተለያዩ አደጋዎችን ለመቀነስ ኢትዮጵያ በትኩረት እየሰራች መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ ገለጹ። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ ከ28ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ጉባኤ ጎን ለጎን በተዘጋጀው የዓለም ሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የሚኒስትሮች ውይይት ላይ ተሳትፈዋል። መድረኩ “የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓት ለሁሉም በሚል መሪ ሀሳብ ነው የተካሄደው። ሚኒስትሩ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት በአየር ጠባይ ለውጥ ምክንያት የሚያጋጥሙ የተለያዩ አደጋዎችን ለመቀነስ ኢትዮጵያ በትኩረት እየሰራች ነው ብለዋል። በተለይ ለሚቲዎሮሎጂ ምልከታ የሚያግዙ ዘመናዊ የመረጃ መሰብሰቢያ ጣቢያ እና መሰረተ ልማት በስፋት በመዘርጋት፤ ወቅቱን የጠበቀ ቦታ ተኮር እና ተደራሽ ትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ በመስጠት የአደጋ ተጋላጭነትን የሚቀንሱ በርካታ እርምጃዎችን እየወሰደች መሆኑንም አብራርተዋል። ሚኒስትሩ አክለውም የአደጋ ስጋትን ለመቀነስ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የሚመራ የብሄራዊ አደጋ መከላከል ካውንስል ተቋቁሞ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በመጥቀስ በመድረኩ የኢትዮጵያን ልምድ ማካፈላቸውን ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያሳየችው ለውጥ ለቀጣናውም ሆነ ለአፍሪካ በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው
Dec 3, 2023 147
አዲስ አበባ ህዳር 23/2016 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያሳየችው ለውጥ ለቀጣናውም ሆነ ለአፍሪካ በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው ሲሉ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ጸሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ በዚህ መርሃ ግብር ከ30 ቢሊየን በላይ ችግኞችን መትከሏንም ጠቅሰዋል። በዱባይ እየተካሔደ በሚገኘው 28ኛው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው የአረንጓዴ አሻራና ሌሎች ተሞክሮዎቿን የምታካፍልበት አውደ ርእይ/ፓቪሊዮን/ በሃገራት መሪዎች፣ በጉባኤው ተሳታፊዎች በመጎብኘት ላይ ነው። የኢትዮጵያን የአረንጓዴ አሻራ አውደ ርእይ/ፓቪሊዮን/ የጎበኙት ዋና ጸሀፊው የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ችግርን ከአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንሶች እና መገናኛ ብዙሃን ገለጻ በላይ ችግሩን በተግባር ተከስቶ ማየታቸውን አስታውሰዋል። ቀጣናው በተለይም ባለፉት ሶስት አመታት የጎርፍ እና የድርቅ አደጋዎች ከማስተናገዱ ጋር በተያያዘ ሀገራቱ ችግሩን ለመፍታት የራሳቸውን መፍትሄ መውሰዳቸውን ሲገልጹ ለዚህም የኢትዮጵያ ተሞክሮ በአረአያነት መጠቀሱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ አየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀሳብ አመንጪነት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለቀጣናውም ሆነ ለአፍሪካ በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው ብለዋል። የዱባዩ ጉባኤ ችግሩን ለመቋቋም የተደረጉ ተሞክሮዎች የሚቀርቡበትና ግብዓት የሚወሰድበት ነው ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ ኢትዮጵያ ያቀረበችው መካነ ርዕይ ችግሩን ለመፍታት የፈጠረችው የህዝብ ንቅናቄው ወደ ውጤት መቀየሩን ያረጋገጠ እንደሆነ ተናግረዋል። በዚህም ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ክስተትን ለመቅረፍም ከ30 ቢሊየን በላይ ዛፎችን መትከሏን ተናግረዋል። ይህም ከዓለም የገንዘብ ተቋማት ምንም አይነት የገንዘብ ድጋፍ ሳትሻ መሪዎቿ ህዝብን በማነቃነቅ ለአካባቢ ጥበቃ በማዋል ለቀጣናው ሀገራት ጭምር ዛፎችን መስጠታቸውን ተናግረዋል። አፍሪካ ባልፈጠረችው የተዛባ ተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም ለአየር ንብረት ለውጥ ችግር መዳረጓን ከማስረዳቷም ባለፈ ኢትዮጵያ ከኢጋድ ጋር በመሆን አፍሪካን ወክላ ለጉዳቱ ማካካሻ ፈንድ በማምጣት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ማድረጓን ጠቅሰዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
መካከለኛ ገቢ ያላቸው የአፍሪካ ሃገራት በሰው ሃብት ልማት ላይ ትኩረት ሊያደርጉ እንደሚገባ ተገለጸ
Dec 7, 2023 79
አዲስ አበባ ፤ ህዳር27/2016(ኢዜአ)፡- መካከለኛ ገቢ ያላቸው የአፍሪካ ሃገራት ፈጠራን ማእከል ያደረገ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት እንዲያመጡ በሰው ሃብት ልማት ላይ አተኩረው ሊሰሩ እንደሚገባ ተመለከተ። በአፍሪካ መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሃገራት በሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች ዙሪያ በፖሊሲ አውጭዎች፣ በምሁራን እና የልማት አጋሮች እና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ትብብር በተዘጋጀው የበይነመረብ የውይይት መርሃግብር ላይ እንደተገለጸው የሰለጠነ ሰው ሃብት አቅም በሚፈለገው ደረጃ አለመገኘት እና የመንግስት እዳ መጨመር መካከለኛ ገቢ ያላቸው የአፍሪካ ሃገራት ዋነኛ ተግዳሮቶች ናቸው ተብሏል። በተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን የሰሜን አፍሪካ ዳይሬክተር ዙዛና ብሪክሾቫ ሽዊድሮዊስኪ “ ሃገራት በሰው ሃብት ክህሎት ላይ በትኩረት መስራትና የትምህርት ስርአታቸውን ከጊዜው ጋር ማራመድ አለባቸው” ያሉ ሲሆን “ከአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ጋር ተዋውቆ ምን፣ እንዴት፣ የትና መቼ መስራት እንዳለበት የተገነዘበ ዜጋ የሚፈጥሩ ከሆነ ካሉበት ማነቆ ፈጥነው መውጣት ይችላሉ” ሲሉ መክረዋል። ወቅቱ የሚጠይቀውን የሰለጠነ የሰው ሃይል ማቅረብ ያልቻሉት የአፍሪካ ባለ መካከለኛ ገቢ ሃገራት ፈጠራን ማእከል ያደረገ እድገት ለማምጣት እየተቸገሩ መሆኑን ይፋ ያደረገው የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ሃገራቱ የሚፈለገውን ለውጥ እንዲያስመዘግቡም የሰው ሃብታቸው ላይ ከወዲሁ መስራት አማራጭ የማይገኝለት መፍትሄ ነው ብሏል። አራተኛውን የኢንዱስትሪ አብዮት ተቀላቅሎ ባለከፍተኛ ገቢ የመሆን ርእይ ያላቸው ሃገራት መዋቅራዊ ሽግግራቸውን በዘላቂነት ለማሳካት ያግዙናል የሚሏቸውን አዳዲስ ፈጠራዎችና ወቅቱ የሚሰጣቸውን እድሎች አሟጠው መጠቀም እንዳለባቸውም ኮሚሽኑ መክሯል። ከሌሎች ሃገራት አንጻር እነዚህ ሃገራት መንግስታዊ የእዳ ጫናቸው እያደገ በመምጣቱ ዘላቂ እድገትና ልማት ማስመዝገብ ብሎም ዘላቂ የልማት ግቦችን በማሳካት የዜጎቻቸውን ህይወት በአስተማማኝ ሁኔታ የመቀየር ጥረታቸው እየተገደበ መሆኑን ያተተው ዘገባው ሃገራቱ አሁን ባለው የገንዘብ ስርአት እምነት እንዲያጡ እያደረጋቸው መሆኑንም አንስቷል። በዚህ ጉዳይ ላይ ምሁራን ተመራማሪዎች ፖሊሲ አውጭዎች እና የልማት ባለድርሻዎችን በማካተት ሰፋ ያለ የምክክር ጉባኤ በሞሮኮዋ ማራካሽ ለማድረግ ለሚመጣው የካቲት ቀጠሮ መያዙንም የዥንዋ ዘገባ አመልክቷል፡፡
የኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀል ከሩሲያ ጋር ያላትን ትብብር ያጠናክራል - ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን
Dec 5, 2023 218
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2016(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀሏ ከሩሲያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ገለጹ። በሩሲያ ፌዴሬሽን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ቻም ኡጋላ ኡሪያት የሹመት ደብዳቤያቸውን ለሩሲያው ፕሬዝዳንት አቀርበዋል ፡፡ አምባሳደሩ የሹመት ደብዳቤያቸውን ባቀረቡበት ወቅት ፕሬዝዳንት ፑቲን ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያና ሩሲያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከመሰረቱ 125 ዓመታትን ያስቆጠሩ ወዳጅ አገራት መሆናቸውን አንስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በሩሲያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት በማድረግ የተለያዩ የትብብር ስምምነቶች መፈረማቸው ግንኙነቱን ከፍ ወዳለ ደረጃ እንዳሻገረው መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀሏ ደግሞ የሁለቱን ሃገራት ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተናግረዋል፡፡
በታንዛንያ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት የ47 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ
Dec 4, 2023 123
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 24/2016 (ኢዜአ) ፦ በታንዛንያ ከባድ ዝናብ መጣሉን ተከትሎ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት በትንሹ የ47 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል። የአየር ንብረት ለውጥን ተከትሎ ከፓስፊክ ውቅያኖስ የሚነሳው ዝናብ አዘሉ የአሌ ኒኖ ክስተት ታንዛንያን ጨምሮ በኬኒያና በሶማልያ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል። በሰሜን ታንዛንያም ከቅዳሜ ጀምሮ እየጣለ የሚገኘው ነፋስ የቀላቀለ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሸራተት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ዘጋርዲያን በዘገባው አስነብቧል። በሰሜናዊ ታንዛንያ ካቴሽ ከተማ በተከሰተው አደጋ እስከ ትላንት ምሽት ድረስ በተንሹ የ47 ሰዎች ህይወት ማለፉንና 85 ሰዎች መጎዳታቸውን ተጠቅሷል። በግዛቲቱ እየጣለ የሚገኘውን ነፋስ የቀላቀለ ዝናብ ተከትሎ የተጎጂዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ያመለከተው ዘገባው ለአካባቢው ነዋሪዎች የማስጠንቀቂያ መልዕክት ከግዛቲቱ የአደጋ መከላከል ኮሚሽን መተላለፉንም ገልጿል።
የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ከ 12 ሆስፒታሎች አንዱን የመዝጋት አደጋን ደቅኗል
Dec 4, 2023 123
አዲስ አበባ፤ ህዳር 24/2016 (ኢዜአ)፦የካርበን ልቀትን መቆጣጠር ካልተቻለ በአለማችን ካሉ 12 ሆስፒታሎች አንዱ በአየር ንብረት ቀውስ ሙሉ በሙሉ አለያም በከፊል የመዘጋት አደጋ መደቀኑን ጥናት አመለከተ። ይህ ጥናት የቀረበው በዱባዩ ኮፕ28 የመሪዎች የጤና ጉባኤ ላይ ነው። የካርበን ልቀትን መቆጣጠር ካልተቻለ በሚያስከትለው የአየር ንብረት ቀውስ በአለማችን ካሉ 12 ሆስፒታሎች አንዱ ሙሉ በሙሉ አለያም በከፊል የመዘጋት አደጋ አንደተደቀነበት የሲተቪ ኒውስ ዘገባ ያመለክታል። በክሮስ ዲፔንዳንሲ ኢኒሼቲቭ የሳይንስና ቴክኖሎሊ ዳይሬክተር ዶክተር ካረለ ማሎን በኮፕ 28 ዱባይ የጤና ጉባኤ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳመለከቱት ለጥናት ከተወሰዱ ከ200ሺ 216 ሆስፒታል ናሙናዎች ከ12 አንዱ አደጋላይ ነው ። የአየር ንብረት ለውጡ ሆስፒታሎች ላይ የሚያስከትለው አውሎ ንፋስ፣ የጎርፍ መጥለቅለቅ ወይም የደን ቃጠሎ ስራቸውን ያስተጓጉላል አለያም ወደ ሌላ ቦታ እንዲቀይሩ ያስገድዳቸዋል እንደ ሪፖርቱ ገለጻ። ችግሩን መቅረፍ ካልተቻለም በምእተአመቱ መገባደጃ የአለማችን 16ሺ245 ሆስፒታሎች በአየር ንብረት ለውጡ ሙሉ በሙሉ አለያም በከፊል ይዘጋሉ ። የአየር ንብረት ለውጥ በጤና ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስም የቅሪተ አካላት ነዳጅ አጠቃቀምን መቆጣጠር አስገዳጅ ነው።
ሐተታዎች
ኢትዮጵያዊነት-በህብር የተሳሰረ አንድነት
Dec 7, 2023 63
ኢትዮጵያዊነት-በህብር የተሳሰረ አንድነት ሀገር በጋራ ታሪክ፣ ባህል፣ እሴት፣ መነሻና መድረሻ ተሳስሮ በተወሰነ ግዛት በሚኖር ህዝብ ይመሠረታል። የሀገርን ትርጉም በሚገባ የተገነዘቡ ሰዎች በቤት ይመስሉታል። አንድን ቤት የሚያቆሙት ማገር፣ ወራጅ፣ ቋሚ እንዲሁም ጣራው በአንድ ላይ ተሰናስለው ነው። ልክ እንደ ቤት ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች፤ ሁሉም ባህሎች፣ ታሪኮችና እሴቶች እያንዳንዳቸው ሰበዝ ሆነው ሲደመሩ አገር ይሆናሉ። ገጣሚ፣ ፀሐፊ ተውኔት፣ ሃያሲ እና የሥነ ጽሑፍ ምሁር ደበበ ሰይፉ “የአክሱም ጫፍ አቁማዳ” በሚል ርእስ በፃፈው ግጥም መደምደሚያው ላይ የሚከተለውን አስፍሯል። “እኔና ወንድሞቼ ሁላችን . . . ሁላችን፣ ከባዶ አቁማዳ ነው እሚዛቅ ፍቅራችን፣ ይህ ነው አንድነታችን፣ ይህ ነው ባህላችን፣ ዘመን ማዛጋቱ በያንደበታችን። በዚህ ግጥም ውስጥ የኢትዮጵዊነት ትርጉም ፍንትው ብሎ ይታያል። የህዝቡ መተዛዘንና መደጋገፍ ምን ያህል ጥልቀት ያለው መሆኑን አጉልቶ ያሳያል። ገጣሚ ደበበ ሰይፉ ከዛሬ 30 ዓመት በፊት የፃፈው ጹሁፍ ዛሬ ላይ ደርሰን በአንዳንድ አካባቢዎች የሚታየው የመገፋፋትና የመጠላላት አባዜ ስንመለከት ምን ያህል ወደ ኋላ የሚጎትተን አሰተሳሰብ መሆኑን በግልጽ ያመለክታል። ኢትዮጵያዊነት በህብር የደመቀ፣ በአብሮነት የዘለቀ፣ በጋራ ለመበልጸግ የሚያልምና ነገን አሻግሮ የሚያይ የማህበረሰብ ውጤት ነው፡፡ አባቶቻችን ከወራሪ ጠላት ታግለው የአገራቸውን ነፃነት በደማቸው አስከብረው ለዛሬ ትውልድ ያሸጋገሩት በዚህ መንፈስ ነው። ይህንን ዘመናትን የተሻገረ የጋራ እሴት ለትውልድ ማሸጋገር ከአሁኑ ትውልድ ይጠበቃል። የኢትዮጵያውያንን የጋራ እሴቶች ለመጪው ትውልድ ለማሸጋገር ከሚያስችሉ ኩነቶች መካከል አንዱ በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን የሚከበረው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ነው። ይህ ዕለት የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች የጋራ ጥቅምና አመለካከት እንዳላቸው በማመን ለአንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ግንባታ ማሰሪያ እንዲሆነን የቃል ኪዳን ሰነድ የሆነው ህገ መንግስት ያጸደቁበት ነው። የኢፌዴሪ ህገ መንግስት የጸደቀበትን ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም አስመልክቶ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ተብሎ መከበር ከጀመረ እነሆ ዘንድሮ ለ18ኛ ጊዜ ነው። የዘንድሮውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን “ብዝሃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተከበረ ይገኛል። የዚህ ቀን መከበር የእርስ በርስ ትስስርን ከማጠናከሩም ባሻገር ለብዝሃ ማንነቶች እውቅናን ያጎናጽፋል። በዓሉ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ሊኖራቸው የሚገባ መስተጋብር በመቻቻል፣ በመከባበርና በመረዳዳት እንዲሁም በፍትሐዊነት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን በህዝቦች እምቅ ባህላዊ እሴቶች የተገነባና ከትውልድ ትውልድ በቅብብሎሽ እንዲሸጋገር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) 17ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በተከበረበት ዕለት ባስታለፉት መልእክት “ይህ ቀን የሁላችን ታሪክ፣ የሁላችን ቅርስ የሁላችን እሴት የኢትዮጵያ ሀብትና ኩራት ሆኖ የሚታይበት ሁላችን ለኢትዮጵያ እጅግ አስፈላጊ መሆናችንና በኢትዮጵያ ጥላ ሥር ውበታችን ሞልቶ የሚታይ መሆኑን የምንማርበት ዕለት ነው” ሲሉ ገልጸዋል። ዘንድሮ የሚከበረው የብሔር ብሐረሰቦች ቀን ከህዳር 25 ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች እንዲከበር በማድረግ ብዝሃነትን ያማከለ የአብሮነትና የወንድማማችነት እሴቶችን ለማጠናከር በሚያስችል እሳቤ እየተከበረ ይገኛል። በዚህም መሠረት ህዳር 25 የወንድማማችነት ቀን፣ ህዳር 26 የብዝኀነት ቀን፣ ህዳር 27 የአብሮነት ቀን፣ ህዳር 28 የመደመር ቀን እንዲሁም ህዳር 29 የኢትዮጵያ ቀን በሚል መሪ ሐሳብ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ ከላይ የተገለጹት መሪ ሃሳቦች የተለያዩ ግን ደግሞ በይዘት አንድ የሆኑ የወንድማማችነትንና የአብሮነትን እሴቶች የሚያጎሉ ናቸው። ጠለቅ ተብለው ሲታዩ ሁሉም የአንድነትን መንፈስ የሚንጸባረቅባቸው ሲጠቃለሉም ኢትዮጵያዊነትን የሚያጎሉ ናቸው። በዓሉን ለማክበር የተለያዩ ብሄረሰቦች የየራሳቸውን ባህል በቦታው ተገኝተው ለማስተዋወቅ ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ በተጨማሪ በጉዞአቸውም ላይ ባሉ ከተሞችና አካባቢዎች ላይ እይታን በመፍጠር እርስ በርስ ይበልጥ እንዲተዋወቁም ዕድል ይፈጥራል፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከአብሮነት ይልቅ የተናጠል ተረክ ያነገቡ ዋልታ ረገጥ እሳቤዎች በተለያዩ አካባቢዎች ይስተዋላሉ። በጋራ መኖርን ሳይሆን መገፋፋትን የሚመርጡ፤ በራሳቸው አጀንዳ ሳይሆን በሰዎች አጀንዳ የተገዙ በንጹኃን ደም ፖለቲካ ሰራን ብለው የሚያስቡ ጥቂት ግለሰቦችና ቡድኖች አሉ። ይህን አስተሳሰብ የሚያቀነቅኑ ቡድኖች በትናትና ላይ የቆሙ፤ ከትናት መላቀቅ ያልቻሉና ነገን ማሰብ የማይችሉ ናቸው። የኢትዮጵያ ብልጽግና እና ልዕልና የሚመነጨው ከእውነትና ፍቅር ነው። ከግራም ከቀኝም ያሉ ዋልታ የረገጡ እሳቤዎች ለኢትዮጵያ የሚበጁ አይደሉም። ኢትዮጵያውያን በዋልታ ረገጥ እሳቤ ለሚፈጠሩ አጀንዳዎች ምላሽ ከመስጠት ይልቅ የአጀንዳውን ባለቤትና ምንጭ ማወቅ ይጠቅማል። ኢትዮጵያ ሰላም እንዳትሆን አዳዲስ አጀንዳ እየፈጠሩ ለሚያውኩ አካላት ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት የኢትዮጵያን ሰላምና አንድነቷን ለማስከበር የሚጠበቅበትን ሚና መወጣት ይጠበቅበታል። ትናንት ያለፈና ያመለጠ ታሪክ ነውና ትናትን ለመማሪያ ብቻ መጠቀም ከቻልን ነጋችን ያማረ ይሆናል። (በሚስባ አወል)
"ድሽታ ግና'' የኣሪዎች የምስጋናና የምርቃት በዓል!
Nov 30, 2023 161
በጣፋጩ ሰለሞን (ኢዜአ) በኦሞ ሸለቆ አካባቢ በማጎ ብሔራዊ ፓርክ አቅራቢያ የሚገኙት አሪዎች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦች ውስጥ ይጠቀሳሉ፡፡ ''ኣሪ ኣፍ'' ወይም ''ኣሪኛ'' የተሰኘ የመግባቢያ ቋንቋም አላቸው፤ ከኦሞቲክ የቋንቋ ነገድ ይመደባል። የኣሪ ማህበረሰብ የኢኮኖሚ መሰረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ አካባቢውም ቆላ፣ ደጋ እና ወይና ደጋ የአየር ጠባይ አለበት። ኣሪዎች የቤት አሰራራቸው፣ የሙዚቃ ጥበባቸው፣ የአጨፋፈር ስልታቸው፣ አለባበስና አጋጌጣቸው እጅግ ማራኪና የቱሪስት ቀልብን የሚስብ ነው። እግር ጥሎት ወደ አካባቢው ያቀና እንግዳ ባይተዋርነት እንዳይሰማው የሚያደርገው የኣሪዎች የእንግዳ አቀባበል ባህል የሚደነቅ ነው። አሪዎች ለቤታቸው እንግዳ የሆነን ሰው ''አቦቶ፤ ደኣይቶ'' - ውይ በሞትኩልህ! እንደማለት ነው እያሉ ደረታቸውን እየደቁ ይቀበላሉ። ለእንግዳው አርደውና አብልተው ሲመሽ ደግሞ እግሩን አጥበው አልጋቸውን ለቀው መሬት አንጥፈው ያስተኛሉ። የራሳቸው የጊዜ ቀመር አቆጣጠር ያላቸው ኣሪዎች ''ሎንጋ'' በተሰኘው የታህሳስ ወር አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት ይቀበላሉ። ይሄው አዲስ ዓመታቸው ደግሞ ''ድሽታ ግና'' የሚል መጠሪያ ያለው ትልቅ ዓመታዊ ክብረ በዓላቸው ነው። የኣሪ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የባህል፣ የታሪክ፣ የቅርስ ጥናትና ልማት የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ዳኜ ገብሬ እንደሚሉት የአዲስ ተስፋና ወንድማማችነት ተምሳሌት የሆነው ድሽታ ግና በማህበረሰቡ ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው በዓል ነው። የብሔረሰቡ የዘመን መለወጫ የሆነው የ"ድሽታ ግና" በዓል የሁለት ቃላት ጥምር ሲሆን ''ድሽታ'' ምስጋና "ግና'' ደግሞ ምርቃትን ይወክላል። የ"ድሽታ ግና" በዓል አርሶ አደሩ የዘራው ዘር ፍሬ አፍርቶ ጎተራው፣ ከብቶች ተዋልደው ጋጥ ሲሞላና ቤቱ በበረከት ሲትረፈረፍ ፈጣሪን የሚያመሰግኑበት፤ በባህል መሪዎች ቡራኬ የሚሰጥበት ታላቅ የምስጋናና የምርቃት በዓል ነው። በባህሉ መሰረትም ወደ አዲሱ አመት ቂምና ቁርሾን ይዞ መሻገር አይቻልም። ስለዚህ ከበዓሉ በፊት በዳይና ተበዳይ "ይቅር" ተባብለው ቂም በቀልን ከአሮጌው ዓመት ጋር ሸኝተው በፍቅር አዲሱን ዓመት እንደሚቀበሉ ነው አቶ ዳኜ የሚናገሩት፡፡ በዚህም መሰረት አንድ የኣሪ ማህበረሰብ አባል በዓሉ ከመድረሱ በፊት "በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ያስቀየምኩት ካለ" በሚል በየቤቱ እየተዟዟረ ይቅርታ ይጠይቃል። በዚህ አጋጣሚ ምናልባት እስከ ህይወት መጥፋት ድረስ የሚደርስ በደል ከተፈፀመ በዳዩ ሽማግሌ ልኮ ፀፀቱን ገልፆ ተበዳይን ተማፅኖ ይቅርታ ይጠይቃል፤ ይቅርታም ይደረግለታል። በየቤቱ ይቅርታ የሚጠይቅበት ምክንያት ቂምና ቁርሾ ወደ አዲሱ ዓመት መተላለፍ ስለሌለበት ነው። ቂምና ቁርሾ በውስጡ ይዞ በዓሉን የሚያከብር አሊያም የበዓል ድግስ ደግሶ ጎረቤት ጠርቶ ማብላት በብሔረሰቡ ዘንድ በጥብቅ የተከለከለ እንደሆነ አቶ ዳኜ ይገልፃሉ። አንድ የኣሪ ማህበረሰብ አባል ዕርቅ ከፈፀመ በኋላ "አርሼ ጥሩ ምርት አግኝቻለሁ፤ ነግጄ አትርፊያለሁ፣ ከብቶቼ ጋጣ ሞልተውልኛል፣ ቤቴ በበረከት ተትረፍርፏል" ሲል ካገኘው ላይ ቀንሶ ድል ያለ ድግስ ይደግሳል። ድግሱ የተራበውን በማብላት፣ የተቸገረውን በመጎብኘት ፈጣሪ ላደረገላቸው በጎ ነገር ከሌሎች ጋር አብሮ ማዕድ በመቋደስ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርብበት እንደሆነም አቶ ዳኜ ይናገራሉ። የ"ድሽታ ግና" በዓል እሸት የሚቀመስበት ነው። በበዓሉ ዕለት የኣሪ ባላባቶች እሸቱን፣ ወተቱን፣ ማሩን ከቀመሱ በኋላ መጪው ዘመን የተባረከ፣ የጥጋብ፣ የሰላምና የጤና እንዲሆን ይመርቃሉ። የሰላምና የአብሮነት እንዲሁም ያለፈውን ዘመን በመተው በአዲስ ተስፋ እጅ ለእጅ በመያያዝ ወንድማማችነትን በማጠናከር ሰርቶ በመለወጥ እና ለሌላው መትረፍን ጭምር የሚያበረታታ በዓል ነው። የብሄረሰቡ ተወላጅ የሆኑት አቶ ፍቃዱ ጋሲ በእንደሚናገሩት፤ የ"ድሽታ ግና" በዓል የፍቅር፣ የአንድነትና የይቅርታ አስተምህሮ ያለው አብሮነትን የሚያጠናክር ነው። በዓሉ የተጣላውን የሚያስታርቅ የተራራቀውን የሚያቀራርብ በመሆኑ በየዓመቱ በጉጉት ይጠበቃል። የዕድገትና ለውጥ መሰረት ጭምር ተደርጎ የሚወሰድ ነው። የዘንድሮውን የ"ድሽታ ግና" በዓልም አብሮነትን፣ አንድነትን፣ መረዳዳትን በሚያጎላ ብሎም የባህሉን እሴት በጠበቀ መልኩ ለማክበር መዘጋጀታቸውን አቶ ፍቃዱ ይገልጻሉ። የ"ድሽታ ግና" በዓል ጠቃሚ ባህላዊ እሴቶች ያሉትና ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ የመጣ ነው። አሁንም በዓሉ ባህላዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር በማስተማር ሃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ነው በአጽንኦት የተናገሩት። የ"ድሽታ ግና" በዓል ከመድረሱ አስቀድሞ እናቶች ከእንሰት እና ከእንስሳት ተዋጽኦ የሚገኙ ለክብር እንግዶችና ለአባ ዎራዎች የሚቀርቡ ባህላዊ ምግቦችን የማዘጋጀት ስራ ላይ እንደሚጠመዱ የገለጹት ደግሞ የብሔረሰቡ አባል ወይዘሮ ደብሪቱ ኣዳዮ ናቸው። ወጣት ሴቶችና ወንዶች ደግሞ ቤት በማስዋብ እና ግቢ በማሳመር ስራ ላይ ይሳተፋሉ። በበዓሉ ወቅትም በቤት ውስጥ የተዘጋጁ ምግቦች በዓይነታቸው ተለይተው ይቀርባሉ። ጥሩ ምግብ ያዘጋጀችና ምግቧ ጣፋጭ የሆነላት ሴት በግጥምና በዜማ ትወደሳለች። የ"ድሽታ ግና" በዓል "የተጣሉትን በማስታረቅ፣ ከተቸገሩ ወገኖች ጋር ቤት ያፈራውን አብሮ በመቋደስ ፣የታመሙትን በመጠየቅ በጋራ የምናከብረው ልዩ በዓል ነው" ያሉት ወይዘሮዋ "ድሽታ ግና" ፍቅር፣ አንድነት እና በጎነት ጎልቶ የሚታይበት ዕለት እንደሆነም ነው የገለጹት። በድሽታ ግና በዓል "በዕርቅ የማይቋጭ ጥል፣ የማይድን ቁስል፣ የማይሽር ጠባሳ የለም" ብለዋል። በነዋሪው ዘንድም ለዘመናት ለዘለቀው ሰላምና አንድነት እንዲሁም ጠንካራ የስራ ባህል መሰረት ነው፡፡ የኣሪ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ኤሊያስ ቃሾ በበኩላቸው፤ በዓሉ ከኣሪ ማህበረሰብ አልፎ ለመላው ኢትዮጵያዊያን የሚሆን "በርካታ ጠቃሚ እሴቶችን በውስጡ የያዘ ነው" ሲሉም ይገልጻሉ። "ድሽታ ግና" ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነትን፣ መረዳዳትን እና አብሮነትን የሚያስተምር ህዝብ ለህዝብ የሚያቀራርብ ዕሴት ያለው በዓል ነው፡፡ የ"ድሽታ ግና" በአል ከጥንት አባቶቻችን ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ በዓል ቢሆንም የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ በመሆኑ ተደብቆ የኖረ ቱባ ባህል መሆኑን አንስተዋል። ሃላፊው እንዳሉት የ"ድሽታ ግና" በዓል ከለውጡ ማግስት በመንግስት በተሰጠው ትኩረትና ባገኘው ዕውቅና የአደባባይ በዓል ሆኖ በመከበሩ "የአገር ውስጥና የውጭ አገራት ቱሪስቶች እንዲጎበኙት በር ከፍቷል" ብለዋል። የ"ድሽታ ግና" በዓል እንደ ሌሎች ዕውቅና እንዳገኙ ክብረ በዓላት አድጎ፣ ጎልብቶ እንዲሁም ዕውቅና አግኝቶ ከአገራችን አልፎ የዓለም ቅርስ እንዲሆን የመላ ኢትዮጵያዊያንን እገዛ ያስፈልጋል። የዘንድሮው የድሽታግና በዓል ''ድሽታ ግና ለዘላቂ ሰላም እና ለፈጣን ልማት'' በሚል መሪ ሀሳብ በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች በድምቀት እንደሚከበር የተናገሩት ደግሞ የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ናቸው። በዓሉ "የመተሳሰብ፣ የመረዳዳትና የዕርቀ-ሰላም በመሆኑ የተጣላውን በማስታረቅ፣ የተቸገሩ ወገኖችን በመጎብኘትና ማዕድ በማጋራት ይከበራል" ብለዋል። ሰላምና ወንድማማችነትን የሚሰብከው "ድሽታ ግና" የአሮጌው ዘመን ማጠቃለያና አዲሱን ዘመን ብስራት ከአጎራባች ዞኖች እና ከመላው ኢትዮጵያዊያን ጋር ዕሴቱን በጠበቀ መልኩ በአደባባይ በጋራ ለማክበር አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል። የ"ዲሽታ ግና" ዕሴቶች አገር በቀልና በህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ያላቸው መሆኑን ያነሱት ዋና አስተዳዳሪው፤ እንደአገር ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲሁም የብልጽግና ጉዞን ለማጠናከር "ለተወጠኑ ግቦች ስኬት የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ልንጠቀምበት ይገባል" ብለዋል። ከወርሃ ህዳር አጋማሽ ጀምሮ ከቤተሰብ እስከ ኣሪ ባላባቶች ቅደም ተከተሉን ጠብቆ የሚከበረው የ"ድሽታ ግና" በዓል ታህሳስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ የአዲስ ዓመት ብስራት ይታወጅበታል። በዕለቱ በጂንካ ከተማ በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች በድምቀት ይከበራል። ''ዑሳ ዎም ዣዕሼ !'' እንኳን አደረሳችሁ!
ኢሬቻ የአብሮነት ማሰሪያ ሐረግ
Oct 6, 2023 732
ኢሬቻ የአብሮነት ማሰሪያ ሐረግ (አሸናፊ በድዬ) ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ከክረምት ወቅት መለያየትና መራራቅ በኋላ ሰዎች በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! የእውነትና የሰላም አምላክ! ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! ለምድራችን ሰላም ስጥ! ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!" ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 26 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 27 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" (በውሃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን በዓመቱ አጋማሽ ላይ የሚከበረው "ኢሬቻ ቱሉ" ደግሞ በተራራማ ቦታ የሚከበር ነው። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ሲሆን፤ የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመብቃቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ እዝነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። የኢሬቻ በዓል ከገዳ ሥርዓት ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው ሲሆን፤ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ለዘመናት ሲከበር የቆየ በዓል ነው። በዓሉ በዋናነት በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ፤ በቢሾፍቱ ከተማ በሆራ ሀርሰዲ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ታድሞ የሚከበር ቢሆንም በተለያዩ የኦሮሚያ ዞኖችና ወረዳዎች በድምቀት ይከበራል። የኦሮሞ ሕዝብ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው ፈጣሪ "ዋቃ" ምስጋናውን ለማድረስ የኢሬቻ በዓልን ያከብራል ይላሉ አባገዳዎች። የኦሮሞ ሕዝብ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ የኢሬቻ በዓልን ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲያከብር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይጎርፋል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል። ኢሬቻ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ሲሆን፤ የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ጭምር በመሆኑ ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኦሮሞ ሕዝብ ለሰላም ትልቅ ሥፍራ ይሰጣል። ሰላም ካለ ሁሉም ነገር አለ ብሎም ያምናል። በምርቃቱም "ቡና ፊ ነጋአ ሂንደቢና" ብሎ ይመራረቃል። ቡናና ሰላም አያሳጣችሁ ማለት ነው። ለዚህም ነው በኢሬቻ በዓል ለመላው የሰው ልጅ ሰላምና ደኅንነት ፈጣሪ የሚለመነው። ሳል ይዞ ስርቆት፤ ቂም ይዞ ፀሎት እንዲሉ አበው በኢሬቻ የተጣላ ታርቆ፣ ቂሙን ረስቶ በንጹህ ልቦና ፈጣሪ ንጹህ ወዳደረገው የውሃ አካል ይሄዳል፤ በዚያም ፈጣሪውን ያመሰግናል። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ…………………ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። ብሔር ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ለዚህም ነው ኢሬቻ ከኦሮሞ ሕዝብ አልፎ የመላው ኢትዮጵያውያን በዓልና መገለጫ ነው የሚባለው። በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ አገር የመጡ ልዑካን በዚህ በዓል ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። በዚህ ዓመትም የሦስት ጎረቤት አገራት ልዑካን በዚህ በዓል ላይ እንደሚታደሙ የተገለጸ ሲሆን፤ የኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገራት ተወካዮች እንደሚታደሙ ይጠበቃል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት ትልቅ አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!)
"በገበታ ለትውልድ" የሚለማው የደንቢ ሀይቅ
Oct 4, 2023 694
"በገበታ ለትውልድ" ስለሚለማው የደንቢ ሰው ሰራሽ ሃይቅ ምን ያህል ያውቃሉ? (በቀደሰ ተክሌ ከሚዛን አማን) ደንቢ ሃይቅ ሰው ሰራሽ ሃይቅ ሲሆን በእኛ የዘመን ቀመር በ1970ዎቹ የተሠራ ነው። በተፈጥሮ መስህቦች የተከበበው የደንቢ ሰው ሰራሽ ሃይቅ ለአካባቢው ብርሃንን ይፈነጥቅ ዘንድ የተሰራውን የቀድሞ የደንቢ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብን ተከትሎ የተፈጠረ ሃይቅ ነው። የደንቢ ሃይቅ ለአካባቢው ማህበረሰብ ባለውለታ ነው፤ የመጀመሪያውን የኤሌክትሪክ ብርሃን ያገኙበት ነውና። ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድቡ ከመልክዓ ምድሩ ጋር እንዲስማማ ተደርጎ የተገነባ በመሆኑ ውሃው ከላይ ወደ ታች በሁለት ምዕራፍ ቁልቁል እንዲወረወር ዕድልን ፈጥሮለታል። የመጀመሪያው የኤሌክትሪክ ሃይልን ለማመንጨት በዝግታ የሚወርደው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ሃይል አመንጭቶ ሲወጣ እጅግ ውብ የሆነ ፏፏቴን ፈጥሮ ወደ ታች የሚወርደው ነው። የደንቢ ፏፏቴ ከሃይቁ ወረድ ብሎ ስለሚገኝ "ደንቢ ሃይቅና ፏፏቴ" እየተባለ ይጠራል። ሃይቁን አይቶ ፏፏቴውን ሳያዩ መመለስ የማይቻል ነገር ነው። የደንቢ ፏፏቴ ከላይ ከዓለት ዓለት እየተጋጨ ሲወረወር የሚያሰማውን በግርማ ሞገስ በታጀበ ድምጽ፤ በተራራ ቀበቶ ተገምዶ ወደ ማረፊያ ቦታው ሲምዘገዘግ በለመለመው መስክ ላይ አሻግረው የሚቃኙት የተፈጥሮ ውበት ነው። ያሻው ወደ ተራራው ጫፍ ጠጋ ብሎ እንደ ጢስ በሚተነው የውሃ አካል ፊቱን እያስመታ አልያም ከሃይቁ ፊት ለፊት ራቅ ብሎ ተቀምጠው እየተመለከቱ መንፈስን የሚያድሱበት ውብ የፏፏቴ ሥፍራ ነው። ከላይኛው የግድቡ አናት ወደ ታችኛው ለመውረድ 640 ደረጃዎችን አቆልቁሎ መጓዝን ይጠይቃል። ይህ ትዕይንት ደግሞ የደንቢ ሃይቅ ሌላኛው መስህብ ነው። የደረጃዎቹን የመውጣትና የመውረድን ድካም አረንጓዴ ካባ የደረበው የሥፍራው ልምላሜ እንዲዘነጋ ያደርጋል። የደንቢ ሃይቅ አካባቢ ቀልብን ስቦ ድካምና ሌላ ሃሳብን አስትቶ ሃሴትን የሚያጎናጽፍ የተፈጥሮ ፀጋን የታደለ ነው። የደንቢ ሃይቅና ፏፏቴ ግርማ ሞገስ ምስጢሩ የአካባቢው ደን ነው። በረጃጅም እድሜ ጠገብ የሃገር በቀል ዛፎች የተከበበ ነው። በእምቅ ደኑ ውስጥ የሚገኙ አዕዋፋት ለሚገባ ለሚወጣው ሁሉ እንደየ ፀጋቸው ያዜማሉ። ጉሬዛዎችና ጦጣዎች ከዛፍ ወደ ዛፍ እየዘለሉ እጅ ይነሳሉ። ይህ አካባቢ የተጎናጸፈው የቱሪዝም ፀጋ ከብዙዎች ዐይን ርቆ ቆይቷል። አሁን ግን በቃ ብሎ ሚሊዮኖች ሊጎበኙት ጊዜው ተቃርቧል። አካባቢው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምሥረታን ተከትሎ ወደ ሥፍራው ጎራ ለሚሉ ሚኒስትሮችና የሃገር መሪዎች የማስተዋወቅ ሥራ በመሠራቱ "የገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክት አንዱ አካል ሊሆን ችሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ቦታው ድረስ በመሄድ፣ በማየትና ለዓለም ጭምር በማስተዋወቅ የደንቢ ሎጅ ግንባታን የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል። በመድረኩ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የሚለማው የደንቢ ሃይቅ ሎጅ ፕሮጀክት በአንድ ዓመት ተኩል የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚጠናቀቅ ነው። በተጨማሪም በደንቢ ሃይቅ ሎጅ አቅራቢያም ሌላው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠለት የአየር ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክት ይበልጥ አካባቢውን የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚያስችል ነው። የሎጅ ግንባታው ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባ፤ ደንቢ ላይ ያረፈ ጎብኚ ከ40 በላይ የሚፍለቀለቁ የዑሲቃ ፍል ውሃ ቦታዎችን፣ የጋርንናንሳ ተራራን እና ሌሎች የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ የቤንች ሸኮ ዞን የተፈጥሮ ፀጋዎችን በቅርብ ርቀት መጎብኘት ይችላል። የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሳሙኤል አሰፋ በርካታ የቱሪዝም ሃብቶችን በዙሪያው አቅፎ የያዘው ደንቢ በቅርቡ የቱሪዝም ኢኮኖሚ አነቃቂ ሃይል ይሆናል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በነደፉት የ"ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክት ሲለማ ከሃገር ውስጥ ባሻገር ከሃገር ውጭ በርካታ ጎብኚዎችን በማስተናገድ የውጭ ምንዛሬ የሚገኝበት ፕሮጀክት መሆኑንም ሳይዘነጉ። እንደዚህ አይነት ሃገራዊ ፕሮጀክቶች በአካባቢያቸው የተለመዱ አለመሆናቸውን ጠቅሰው የመንግስትን እይታና በአካባቢው ያለውን ሃገራዊ አቅም ወደ ኢኮኖሚ ለመቀየር ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑንም አድንቀዋል። የቤንች ሸኮ ዞን በርካታ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ መስህብ ሃብቶች እንዳሉት ገልጸው የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያለውን ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመቀላቀል መንግስት የከፈተውን መልካም አጋጣሚ መጠቀም እንደሚገባ ነው የጠቆሙት። ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት መሠረት ተቀምጦለት እየተገነባ ያለውን የሚዛን አማን ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ግንባታን መልካም አጋጣሚውን ለመጠቀም አንዱ ዕድል እንደሆነም ጠቅሰዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ ለመጎብኘት የሚመጡ እንግዶችን ቆይታ ለማራዘም እና ወደውት ተደስተው እንዲመለሱ ለማስቻል ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እናደርጋለን ያሉ ሲሆን በቅርብ ርቀት ያሉ የቱሪስት መዳረሻዎችን ምቹ የማድረግ ሥራም በትኩረት ይከናወናል ብለዋል። የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪው አቶ ያሬድ ካንጃ ደንቢ በቅርብ ርቀት ቢገኝም ያልለማ በመሆኑ ብዙዎች የመጎብኘት ዕድል እንዳላገኙ ተናግረዋል። ደንቢ ሃይቅ እና ፏፏቴ ከሃይቅነትና የቱሪስት መስህብነት ባሻገር በሥራ ዕድል ፈጠራም ጭምር ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አለው ነው ያሉት። የሎጁ መገንባት የዞኑን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ወደ ዓለም ገበያ ያስገባል የሚል ተስፋ መሰነቃቸውንም አቶ ያሬድ አልሸሸጉንም። "እንደ አካባቢው እምቅ የተፈጥሮ ሃብት አቅም አንጻር ይህ ጅምር ነው፤ በቀጣይ በርካታ ፕሮጀክቶችን እንጠብቃለን" ብለዋል።
ትንታኔዎች
ከገበታ ወደ ገበያ
Sep 24, 2023 678
(ሰለሞን ተሰራ) ኢትዮጵያ ከ10 ሺ ዓመታት በፊት ከኒዮሊቲክ አብዮት ዘመን ጀምሮ የበርካታ አዝእርትና እንስሳት ሀብት መፍለቂያ ሆና ዛሬ ላይ ደርሳለች። ከዚያ ዘመን ጀምሮ የአገራችን ገበሬ በስራ ያካበተውንና በተፈጥሮ የተሰጠውን ችሎታ በመጠቀም ዘመናዊና ቴክኖሎጂ በወለዳቸው መሳሪያዎች ሳይታገዝ፣ በየጊዜው የአፈሩ ለምነት እየቀነሰ ከሄደው መሬትና ባህላዊ የአስተራረስ ዘዴ ጋር እየታገለ ቁጥሩ እየናረ የሚሄደውን ህብረተሰብ ከመመገብ ወደ ኋላ ብሎ አያውቅም። ግብርናው ከቀደሙት ጊዜያት በተለየ ሁኔታ ትኩረት ባገኘበት በዚህ ዘመንም ከተደቀኑበት እጅ ጠምዛዥ ጉዳዮች ጋር ግብግብ ውስጥ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ ድርቅ፣ የፖለቲካና የገበያ አለመረጋጋት፣ የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ውስንነት፣ የተፈጥሮ አደጋ፣ የዘርፉ ኢንቨስትመንት አለመዳበር የዘርፉ ተግዳሮት ሆነው ቀጥለዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በ78ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ባደረጉት ንግግር በተለይ የአየር ንብረት ለውጥን ተጽእኖ በሚገባ አመላክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ በተለይ በአፍሪካና በሌሎች በማደግ ላይ ያሉ አገራት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ቀውስ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ እንዲበጅ እየሰራች መሆኗን ተናግረዋል። በተለይ ኢትዮጵያዊያን ከጫፍ ጫፍ እየተሳተፉበት ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የዚህ ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ላለፉት ተከታታይ አራት ዓመታት በሰራችው ስራ በአካባቢ ጥበቃና በግብርናው ዘርፍም ውጤት ማግኘቷ እሙን ነው። ነገር ግን ፈተናዎቹን በድል ለመሻገር የሚደረጉ ጥረቶችና በዘርፉ የተገኙ አበረታች ውጤቶች እንደተጠበቁ ሆነው አሁንም ዘርፉን በሰለጠነ የሰው ሃይል፣ በተደራጀ የግብርና መሳሪያና ማቀነባበሪያ በመደገፍ አገርና ህዝብ ከግብርናው ዘርፍ ማግኘት ያለባቸውን ጥቅም እንዲያገኙ ለማስቻል ብዙ መስራት ይጠይቃል። በተለይ የግብርና ሜካናይዜሽንን ከማስፋፋትና ዘመናዊ የግብርና ግብዓቶችን በበቂ ሁኔታ ከማቅረብ አኳያ መንግስት እየሰጠ ያለው ትኩረት የበለጠ መጠናከርና ማደግ ይኖርበታል። የግብርናና የገጠር ልማት የፋይናንስና ብድር አቅርቦትን ማጠናከር እንዲሁም የአካባቢና ስነ ምህዳር ጥበቃ ስራዎችን በዘላቂነት መተግበር ያሻል። በተለይ ኢትዮጵያ በልዩ ትኩረት እየሰራችበት ያለውን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ጉዳይ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብርና አሰራር በመቀየርና አማራጮችን በማማተር እውን ማድረግ ይጠይቃል። ኢትዮጵያ በዝናብ ወይም በመስኖ መልማት የሚችል ያልተነካ ሰፊ መሬት እንዳላት የሚታወቅ ሲሆን ይህን ያልታረሰ መሬት በአግባቡ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ አንዱ አማራጭ ነው። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ግብርናው ከ34 በመቶ በላይ የጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት ድርሻ ይዟል፡፡ በተጨማሪም ዘርፉ 79 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች መተዳደሪያ ሲሆን በተመሳሳይ 79 በመቶ የሚሆነውን የውጭ ንግድ ገቢ በመሸፈንና ለአገር ውስጥ ኢንቨስትመንትና ገበያ የጥሬ እቃ አቅራቢ በመሆንም ይታወቃል። መንግስት በግብርናው ዘርፍ የወሰዳቸው የሪፎርም ስራዎችና ግብርናን ከአረንጓዴ አሻራ ጋር በማስተሳሰር የሰራቸው ስራዎች ፍሬ ማፍራት ጀምረዋል። በተለይ የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የተሰራው ስራ ቀዳሚ ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ብቻ የስንዴ ምርታማነቷን በ27 በመቶ ማሳደግ መቻሏ ስንዴ ከመሸመት ወደ መላክ የመሸጋገሯ ማረጋገጫ ሆኗል። በጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ አህመድ የተጀመረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በዚህ ረገድ የሚታይ ለውጥ እያሳየ ሲሆን በተሰራው ውጤታማ ስራ ባለፈው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ከውጭ ስንዴ አላስገባችም። በዚህም 1 ቢሊዮን ዶላር ማዳን መቻሏን የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ በቅርቡ ማሳወቃቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት 15 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቶን ስንዴ ያመረተች ሲሆን በተያዘው ዓመት ደግሞ ምርቱን ወደ 19 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቶን ለማሳደግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል። ይህንኑ ግብ ለማሳካት ደግሞ የስንዴ ማሳዋን በማሳደግ 5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል ለመሸፈን እየሰራች ነው። ከዚህ ውስጥ በመስኖ የሚለማ ስንዴን በ2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ በመዝራት በመስኖ የሚለማውን ስንዴ በ54 በመቶ ለማሳደግ እየሰራች ነው። ይህ ደግሞ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርቱን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እንደሚያስችል ዶክተር ግርማ አመንቴ ተናግረዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ያወጣው ሪፖርት እንደሚያመላክተው የግብርናው ዘርፍ በአስር ዓመቱ የልማት ዕቅድ የመጀመሪያዎቹ 3 ዓመታት (2013-2015) በዋና ዋና ተግባራት ከዕቅድ በላይ ዕድገት አስመዝግቧል። በዚህም ዘርፉ በ2013 ከነበረበት 5 ነጥብ 1 በመቶ በ2014 ወደ 5 ነጥብ 8 በመቶ ያደገ ሲሆን በ2015 ደግሞ 6 ነጥብ 3 በመቶ እድገት አስመዝግቧል። ግብርናውን ለማሳደግ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው የሰብል ምርት ሲሆን ለዘርፉ ማደግ 65 ነጥብ 5 በመቶ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ደን ልማት 8 ነጥብ 6 በመቶ እንዲሁም የእንሰሳት ሃብት ልማቱ 25 ነጥብ 9 በመቶ ድርሻ ይዘዋል። በ2015 ዓ.ም ጠቅላላ 627 ሚሊዮን ኩንታል ሰብል ለማምረት ታቅዶ ከተቀመጠው ግብ በላቀ ደረጃ 639 ሚሊየን ኩንታል ምርት ማግኘት ተችሏል። ከበጋ ስንዴ ልማት ጎን ለጎን በቅርብ ጊዜ የተጀመሩ የቡና፣ አቮካዶና አኩሪ አተር የመሳሳሉት ትላልቅ የግብርና ልማት ስራዎች በተመሳሳይ ውጤት ታይቶባቸዋል። የአዝርት፣ የአትክልት፣ ፍራፍሬና ስራስር ምርት ከፍተኛ የዕድገት ሽግግር የታየባቸው ናቸው። በአረንጓዴ አሻራ፣ በሌማት ትሩፋትና በከተማ ግብርና ተሞክሮ ሊወሰድበት የሚችል አፈጻጸም መመዝገቡ በሪፖርቱ ተመላክቷል። ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን የስንዴ ምርት ከውጭ ገበያ ስትገዛ የኖረች ሲሆን በተለይም በተለያዩ ጊዜያት የሚፈጠሩ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች አቅርቦቱን ሲያስተጓጉሉት ቆይተዋል። አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ የስንዴና የገብስ ምርትን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት የቻለች ሲሆን የሩዝ ፍላጎቷን ደግሞ 50 በመቶ መሸፈን ችላለች። በስንዴ ምርታማነት የተገኘውን ተሞክሮ ወደሌሎች ሰብሎች በማስፋት የገቢ ምርቶችን በቀጣይ ለመተካት በትኩረት እየተሰራበት ይገኛል። ይህንን ለማሳካት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ እንደሚሆን ይታመናል። በተለይ ለግብርና ዘርፉ የተሻለ በጀት መመደቡ፣ እስካሁን ለመጣውና ለወደፊትም ይመጣሉ ተብለው ለሚታሰቡ ለውጦች ትልቅ ምክንያት ነው። ለምሳሌ የ2015 ዓ.ም. በአገሪቱ ለተለያዩ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልማት ከተመደበው 786 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በጀት ውስጥ፣ ለግብርናው ዘርፍ 34 በመቶ የሚሆን በጀት ተመድቧል። ይህ ደግም ከለውጡ በፊት ከአሥር በመቶ ያልበለጠ በጀት ጋር ሲነፃፀር እጅግ ከፍተኛ ያደርገዋል። በተጨማሪም መንግሥት ለኩታ ገጠምና ለመስኖ እርሻ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱ፣ ሙሉ በሙሉ በዝናብ ላይ ጥገኛ የሆነውን የግብርና ስራ በመስኖ የታገዘ እንዲሆንና አርሶ/አርብቶ አደሩ በዓመት ከአንድ ጊዜ በላይ እንዲያመርት ማድረጉ ውጤቱን ጉልህ አድርጎታል። እንደ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ሩዝ፣ ቡና፣ አቦካዶ ሁሉ በግብርና ሚኒስቴር ከተያዙና በልዩ ትኩረት ከሚከናወኑ ዕቅዶች አንዱ የማር ምርትን ማሳደግ ሲሆን፣ በአሥር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ እንደተመላከተውም የማር ምርትን በማዘመን ምርቱን ለማሳደግ በስፋት ይሰራል። በኢትዮጵያ ለማር ምርት ተስማሚ የሆነ አግሮ ኢኮሎጂና ብዛት ያላቸው ዕፅዋት መኖራቸው የሚመረተው ማር የተፈጥሮ ጥራት እንዲኖረው ያግዛል። ይህንኑ ዕምቅ ሀብት ትኩረት ሰጥቶ ማልማት ከተቻለ ከ500 ሺሕ ቶን በላይ ማርና ከ50 ሺሕ ቶን በላይ ሰም ማምረት እንደሚቻል ባለሙያዎች ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እንስሳት ሀብት ኢንስቲትዩት ባወጣው መረጃ በሀገሪቱ አለ ተብሎ ከሚገመተው ሰባት ሚሊዮን የንብ መንጋ ውስጥ 90 በመቶው በባህላዊ ቀፎ ውስጥ የሚገኝ ነው። የንብ መንጋዎቹ በባህላዊ ቀፎ ከመኖራቸው በተጨማሪ በጫካ መገኘታቸው ሃብቱ ለአገር ዕድገት በሚፈለገው ልክ እንዳይውል አድርጎታል። ያም ቢሆን ባለፈው ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተጀመረው “የሌማት ትሩፋት” ለማር ምርት ትኩረት የሰጠ በመሆኑ ዘመናዊ የንብ ማነብ ዘዴ እንዲስፋፋ ተደርጓል። በዚህም የማር ምርታማነትን በዓመት ወደ 98 ሺህ ቶን ማሳደግ መቻሉ በቅርቡ መገለጹ ይታወሳል። ምርቱን በእጥፍ ለማሳደግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑም እንዲሁ። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የማር ምርት የማምረት አቅም ካላቸው አሥር ሀገሮች አንዷ በመሆኗ ሃብቱን ለማልማት ሁሉም ሊረባረብ ይገባል። በአጠቃላይ መንግሥት ለአረንጓዴ ልማት/አሻራ፣ ለአፈርና አካባቢ ጥበቃ የሰጠው ትኩረት ሁሉን አቀፍ የግብርና ዕድገት እንዲመጣ መሠረት ሆኗል። በተጨማሪም መንግስት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሌማት ትሩፋትና ምግባችን ከደጃችን መርሐ ግብር ኅብረተሰቡ የከተማ ግብርናን እንዲያስፋፉ በገጠርም ሆነ በከተማ ያከናወነው ተግባር ውጤት አስመዝግቧል። በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት ዘርፉን ለማዘመን የተከናወኑ የልማትና የሪፎረም ሥራዎች ግብርናውን ከአዝጋሚ ጉዞ በማውጣት ወደ ፈጣንና አስተማማኝ ጉዞ ማሸጋገር ችለዋል። ኢትዮጵያ አሁንም አያሌ ያልተነኩ ዕምቅ ሀብቶች ያሏት መሆኗን እንደ እድል በመውሰድ ቀጣይነት ያለው እድገት ማስመዝገብ ይጠበቅባታል። ይህን ማድረግ ስትችል የግብርና ሽግግር ይረጋገጣል። ግብርናውን ለማሻገር ደግሞ በፋይናንስ፣ በግብአት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሰለጠነ የሰው ሀይል ልማት ላይ በትኩረት መስራት ያሻል። ወጣቱ ግብርናን እንደ ንግድ (Agri-Bussiness) ማየትና በዚያው ልክ መስራት ይጠበቅበታል። በዚህ ልክ በርብርብ ሲሰራ ግብርናን በማሸጋገር ገበታን ከመሙላት ወይም ከፍጆታ አልፎ ገበያን ማማተር ይቻላል።
ኢትዮጵያ እና መስከረም
Sep 22, 2023 674
(በአየለ ያረጋል) መቼስ ሀገሬው መስከረምን ሲናፍቅ ‘ለብቻ’ ነው። በባህሉ፣ በትውፊቱ፣ በስለ-ምኑ፣ በኪነ-ቃሉ እና ስነ-ቃሉ ልዩ ሥፍራ ይሰጠዋል ለመስከረም። እንደ መስከረም ክብር፣ ሞገስ እና ፀጋ የተቸረው የትኛው ወር ይሆን? ማንም! ሀገሬው ለቆንጆ ልጁ ስም ሲያወጣ ‘መስከረም’ እንጂ በሌላ ወር ሰይሞ ያውቃል? አያውቅም። በኢትዮጵያ ምድር መስከረም ለሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን ለእንስሳት እና አዕዋፋት ራሱ ልዩ ጊዜ ነው። ‘ኢትዮጵያ ነይ በመስከረም…’ እንዲሉ መስከረም ለኢትዮጵያ ውበቷ፣ ቀለሟ፣ ትዕምርቷ፣ የባህር ሃሳቧ መባቻ ነው። ተናፋቂው መስከረም ዝም ብሎ ወር ብቻ አይመስልም። እውቁ ሠዓሊ እና ባለቅኔ ገብረክርስቶስ ደስታ መስከረምን “… በሽቱ መዓዛህ ለውጠው ዓመቱን፤ ይታደስ ያረጀው ፍጥረት ሌላ ይሁን…” ሲል የአዲስ ተስፋና መንፈስ መሻቱን አሳይቷል። ተወዳጇ ድምፃዊት እጅጋየሁ ሽባባው ደግሞ “… መስከረም ለምለሙ፣ መስከረም ለምለሙ፣ ብሩህ ዕንቁጣጣሽ ደስታ ለዓለሙ…” ትለዋለች መስከረምን ስታዜመው። እንደየ ንፍቀ ክበቡ ዓመታት በወራት ሲመነዘሩ የራሳቸው መልክና መገለጫ አላቸው። ኢትዮጵያም ከጎርጎሮሳዊያኑ የዘመን ቀመር በሰባት ዓመት ከስምንት ወራት ልዩነት ያለው የራሷ የዘመን ቀመር አላት። ኢትዮጵያ ብቸኛዋ ባለ 13 ወራት ሀገር ነች። ወራቱም መጸው(መኸር)፣ ሐጋይ(በጋ)፣ ፀደይ(በልግ) እና ክረምት በሚል በአራት ወቅቶች ይከፈላሉ። ወቅቶቹም የራሳቸው ጸባይ፣ ክዋኔ፣ ትውስታና ትዕምርት ይቸራቸዋል። እያንዳንዱ ወርም እንደዚሁ። ከዘመን መባቻው መስከረም እስከ ማዕዶተ-ዘመኗ ጳጉሜን ወራቱ በሰማይና በምድሩ ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ውቅራቸው ግላዊ ገጽታ ይነበብባቸዋል። የወራቱ ቅላሜ እና ሕብርነት ልዩ መልክዓ-ኢትዮጵያን ይፈጥራል። ‘የ13 ወር ፀጋ’ የሚለው መጠሪያም በ‘ምድረ ቀድምት’ እስኪተካ ድረስ ለብዙ አሥርት ዓመታት መለያ ሆኖ ዘልቋል። ይህን መለያ ስም ያወጡት እና የኢትዮጵያ ቱሪዝም አባት የሚሰኙት አቶ ኃብተሥላሴ ታፈሠ “ኢትዮጵያ የ13 ወራት ፀሐይ ባለቤት ናት። ስያሜው ከምንም የፖለቲካና ሃይማኖት ጋር ንክኪ የለውም” ብለው ነበር። የኢትዮጵያ ወራት ስያሜ ከመልክና ግብራቸው ይመነጫል። የወራት መባቻው መስከረም እንደዛው። ሊቃውንት መስከረምን ሲፈትቱት መስ - 'ዐለፈ፤ ከረመ' ይሉትና “ክረምቱን ማስከረሚያ፤ የጥቢ መባቻ" ወርኅ ሲሉ ያመሰጥሩታል። መስከረም ዘመን ያስረጃል፤ አዲስ ሕይወትና ተስፋ ደግሞ ይደግሳል። አንዳንዴም ይህ ወር ዘመን መለወጫ፣ ዕንቁጣጣሽ፣ ቅዱስ ዮሐንስ ተብሎም ይጠራል፡፡ 'አገር፣ ቀለም፣ ዘመን' እንደሸማው በድርና ማግነት ከሚሰባረቅባቸው ወራት አንዱ መስከረም ነው። መስከረም አገርኛ አለባበስ፣ አገርኛ ዝማሬ፣ አገርኛ ጨዋታ፣ አገርኛ ትውፊትና ቀለም በመስከረም በዓላት በተግባር ይታያል። መስከረም ሁለንተናዊ ውበቱ ድንቅ ነው፤ ትዕምርቱም ጉልህ ነው። የመልክዓ-መስከረም ድምቀት ማሳያዎች ዘመን መለወጫ በኢትዮጵያ ዘመን ስሌት ቀለበት መስከረም 1 ቀን ዘመን ይለወጣልና። የዘመን መለወጫ በዓል ‘ርዕሰ ዓውደ- ዓመት’ ይሰኛል። የባህር ሐሳብ ሊቃውንት መስከረም ለምን የዘመን መለወጫ እንደሆነ ሲያትቱ “ብርሃናት /ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት/ የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው” ይላሉ። በመስከረም ሌሊቱ ከቀኑ እኩል ነው። ደራሲ ካሕሳይ ገብረእግዚአብሔር “ቀዳማይ፣ ርዕሰ ክራሞት፣ መቅድመ አውርኅ፣ ርዕሰ ዐውደ-ዓመት፣ የክረምት ጫፍ መካተቻ፣ የመፀው መባቻ” ይሉታል ወርኃ መስከረምን። እናም ዘመነ ማዕዶቷን፤ ወርኅ ተውሳኳን ‘ጳጉሜን’ ተሻግሮ መስከረምን መሳም ይጓ'ጓ'ል። የመስከረም ጥባት በአያሌው ይሻታል። 'መስከረም ሲጠባ ወደ አገሬ ልግባ …’ እንዲሉ የተሰደዱት በአዲስ ዓመት መባቻ የአገራቸውን አፈር ለመሳም ያማትራሉ። ’አበባዬ ሆይ፤ አበባዬ ሆይ’ የሚሉ ሕፃናት ተስፋና ምኞታቸውን በወረቀት ያቀልማሉ፤ የአበባ ስዕላት ይዘው በየደጃፉ ይሯሯጣሉ፤ የ’ዕደጉ’ ምርቃት ያገኛሉ፤ በደስታ ይንቦጫረቃሉ። በዚህ ድባብ ነው እንግዲህ መስከረምን የግዑዛንም የሕይወታውያንም የነፃነት፣ የተስፋና የፍቅር ወርኅ ተደርጎ የሚናፈቀው። የብዙ ሺህ ዘመናት ባለታሪኳ ኢትዮጵያ ተፈጥሯዊ አዱኛ ሳይርቃት በእርስ በርስ ጦርነት፣ በጠላት ፍላፃዎች እና በድንቁርና ብዛት... ሰንኮፎቿ ሳይነቀሉ በመልከ-ብዙ ምስቅልቅሎሽ ውስጥ ዛሬ ደርሳለች። ጊዜው የኢትዮጵያን መስከረም ያስናፍቃል። ዕንቁጣጣሽ መስከረም በአደይ አበባ የሚያሸበርቅ ወር ነው። የነገረ-ዕንቁጣጣሽ የትመጣ መልከ-ብዙ አተያዮች ይጠቀሳሉ። ለምሳሌ “ዕንቁ – ዕፅ አመጣሽ” ብሎ የአበባ መፈንዳት ለማመላከት እንደሆነ የሚጠቅሱ አሉ። ንግሥት ሳባ /አዜብ/ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን የእጅ መንሻ ይዛ ስትሄድ ንጉሡም “ዕንቁ ለጣትሽ ጌጥ ይሁንሽ” በሚል ቀንና ከሌሊት የሚያበራ ቀለበት ስለሰጣት ነው የሚል አፈታሪክም ይነገራል። የስያሜው መነሻ ያም ሆነ ይህ መስከረም ለመልክዓ-ምድሩ፣ ለሰውና ለእንስሳት ሁሉ ‘ፍስሐ ወተድላ’ የሆነ ወር ነው። በመስከረም ምድር በዕንቁጣጣሽ ትፈካለች፤ በአበቦች ታጌጣለች፤ ውኆች ይጠራሉ። ሰማዩም የክብረ-ሰማይ ብርሃኑን ያጎላል። ጥቁር ደመና ጋቢ ይገፈፋል፤ ክዋክብት እንደፈንዲሻ በዲበ-ሰማይ ይደምቃሉ። ዕጽዋትና አዝዕርት እንቡጦች ይፈነዳሉ። የመብረቅ ነጎድጓድ ተወግዶ የሰላምና የሲሳይ ዝናብ ይዘንባል። እንስሳት የጠራ ውሃ እየጠጡ፣ ለምለም ሳር እየነቸረፉ ይቦርቃሉ። እርሻ የከረሙ በሬዎች፣ ጭነት የከረሙ አህዮች መስከረም አንጻራዊ የእፎይታ ወራቸው ነው። ነጎድጓድ በአዕዋፋት ዝማሬ ይተካል። ንቦች አበባ ይቀስማሉ፤ ቀፏቸውን ያደራሉ። ቢራቢሮ ሳትቀር ‘በመስከረም ብራ ከኔ በላይ ላሳር..’ ብላ ትከንፋለች። በ’ዕንቁጣጣሽ’ ምድር ብቻ አይደለችም የምትዋበው። መስከረም ለሰው ልጆችም በተለይም ለወጣቶች የፍቅር፣ የእሸት እና የአበባ ወር ነው። የሰላም፣ የንጹህ አየር፣ የጤና ድባብ ያረብባል። የጋመ በቆሎ እሸት ጥብስ፤ ቅቤ ልውስ፤ ቅቤ በረካ ይናፈቃል። የተጠፋፋ ዘመድ አዝማድ ይገናኛል። ‘ሰኔ መጣና ነጣጠለን’ ብለው ወርኃ ሰኔን የረገሙ ተማሪዎች ተናፋቂያቸውን ያገኛሉና ‘መስከረም ለምለም’ ብለው ያሞካሹታል። የገበሬው የሰብል ቡቃያ ያብባል፤ እሸት ያሽታል። ጉዝጓዝ ሣር፣ ትኩስ ቡና ይሽታል። ደመራ ወመስቀል ሊቃውንት የደመራን የትመጣን ሲፈትቱ ‘ደመረ፣ ተሰባሰበ’ ይሉታል። ጎረቤት፣ የሩቅ የቅርብ ዘመድ አዝማድ ተደምሮ የሚከውነው ነውና። ነገረ መስቀሉ እምነቱ፣ ባህሉ፣ ትውፊቱ ብዙ ነው። መስቀል በሃይማኖተ-አበው ሀተታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን፣ ለፍጡር የሰው ልጆች ያለውን ጥልቅ ፍቅር የገለጸበት ዓርማ ነው። በዚህም መስቀልን አማኝ ምዕመናን እና ካህናት የደኅንነትና የእምነት ምልክታቸው፤ የርኩስ መንፈስ ማባረሪያ መሳሪያቸው አድርገው ይመለከቱታል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መስከረም 10 ቀን ‘ተቀጸል ጽጌ’ በሚል የክርስቶት መስቀል ግማድ (ቀኝ እጁ ያረፈበት ክፋይ) ከኢየሩሳሌም ተነስቶ ኢትዮጵያ የገባበትን ቀን ታከብረዋለች፤ መስከረም 17 ቀን ደግሞ መስቀሉ የተገኘበትን። መስከረም 16 እና 17 ቀን የሚከበረው የደመራ መስቀል በዓል ከሃይማኖታዊ አስተምህሮው ባለፈ ባህላዊ ትውፊትነቱ የጎላ በመሆኑ በአብዛኛው ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ይናፈቃል። ደመራና መስቀል የአንድነት፣ የፍቅር፣ የይቅርታ፣ አብሮነት፣ የምስጋና፣ የተስፋ… እሴቶች የሚገለጹበት ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ክብረ-በዓል ነው። ደመራ እና መስቀል በዓላት ሃይማኖታዊ የአደባባይ በዓል ቢሆንም እንደየ አካባቢው ባህል፣ መንፈሳዊነት፣ ትውፊት፣ ዕውቀት አገርኛ ህብር ጥበባት የሚጎሉበት፣ አገር የውበት አክሊል የምትደፋበት ዕለት ነው። መስቀል የዓለማችን የማይዳሰስ የኢትዮጵያ ወካይ ቅርስ መዝገብ ሥር ሰፍሯል። በመስቀል አገርኛ ቀለም ይጎላል። 'አገር፣ ቀለም፣ ዘመን' እንደሸማው በድርና ማግነት ይሰባረቃሉ። የባህር ማዶ ጎብኚዎች በአግራሞትና መደነቅ ሲናገሩ ይደመጣሉ። የዕንቁጣጣሽ ተከታይ የመስከረም መልክ ነው መስቀል። የደመራ አደማመር እና ማብራት ሥነ-ሥርዓት በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ተመሳሳይ እንዳልሆነ ደራሲ ካሕሳይ ገብረእግዚአብሔር ይተርካሉ። በትግራይ፣ በጎንደር፣ በወሎ፣ በዋግኸምራ፣ በአዊና በከፊል ጎጃም ደመራ ማታ ላይ ተደምሮ ንጋት ላይ ይለኮሳል። በከፊል ጎጃም፣ በሸዋ፣ በአዲስ አበባ፣ በጉራጌ፣ በጋሞ፣ በወላይታና ሌሎች የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ደግሞ እንደየ አካባቢው ተለምዶ መስከረም 16 ከእኩለ ቀን ጀምሮ እስከ አመሻሽ ድረስ ደመራው ይለኮሳል። መስቀል በአንዳንድ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ርዕሰ ዓውደ-ዓመት ይመስላል። በደቡብ ኢትዮጵያ መስቀል ከሃይማኖታዊ ይዘቱ ባህላዊ ጎኑ ይጎላል። ጉራጌዎች፣ ጋሞዎችና ሌሎችም መስቀልን ከሁሉም በዓላት የበለጠ ይናፍቁታል። የተራራቁ ቤተሰቦች የሚገናኙበት የፍቅር፣ የደስታና የእርቅ በዓል ነው መስቀል። በጋሞ ብሔረሰብ ባህል በዋዜማው ሰው ቢሞት እንኳን በሌሊት ተወስዶ ይቀበራል እንጂ ለቅሶ እንደማይለቀስ ይነገራል፤ ለሰው ብቻ ሳይሆን ለእንስሳቱም ልዩ መኖ እንደሚቀርብላቸው ይነገራል። ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ እንደሚባለው በጋሞዎች ደግሞ ‘ለመስቀል ያልሆነ ዱንጉዛ ይበጣጠስ’ በሚመስል መልኩ የባህል ልብስ አለባበስ እንደሚዘወተር መምህር ካሕሳይ (በሕብረ-ብዕር ድርሰታቸው) ጽፈዋል። መስቀል በጉራጌዎች ዘንድ እንደ አውራው በዓል ይቆጠራል። ለመስቀል ዓመቱን ሙሉ ዝግጅት ይደረጋል። አባወራው ሰንጋ ለመግዛት፣ እማወራ ማጣፈጫውን ለማዘጋጀት፣ ወጣቶች ደመራና ደቦት ለማዘጋጀት፣ ልጆች ምርቃት ለመቀበል የየራሳቸውን ይዘጋጃሉ። ቤተሰብ ወዳጅ ዘመድ የሚጠያየቅበት፣ ለትዳር የደረሱ ሚስት የሚያጩበትና የሚመርጡበት ጥላቻና ቂም በፍቅርና በይቅርታ የሚታደስበት ነው። በጉራጌዎች ዘንድ መስቀል ትልቅ ቦታ ይቸረዋል። መስቀል እንደየአካባቢውና ባህሉ የሚናፈቅበት ዕልፍ ገጽታዎች አሉት። ለምሳሌ እኔ በተወለድኩበት ገጠራማ አካባቢ ያለውን በወፍ በረር እንቃኘው! በደመራ ዋዜማ ቀናት ልጆች ተራራ ለተራራ፣ ወንዝ ለወንዝ፣ ቋጥኝ ለቋጥኝ በልጅነት ወኔና ስስት በመዞር ለደመራ የሚሆን እንጨት፣ አደይ አበባ፣ ደቦት(ችቦ) ያጠራቅማሉ። ልክ መስከረም 16 አመሻሽ ከብቶች ወደ ግርግም ከገቡ የመንደሩ ወጣቶች ወደ ‘አፋፍ’ ይወጣሉ። ደመራ ወደሚደመርባት ሥፍራ። ሁሉም የአንድ ዕድር አባላት ቤተሰብ ተወካዮች ባሉበት እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት የደመራው ሥራ ይጠናቀቃል። ደመራው ሲጠናቀቅ ወደየ ቤታችን እንበታተናለን። (አዲስ አበባን ጨምሮ በከተሞች እንደሚደረገው በመስከረም 16 አመሻሽ ደመራው አይለኮስም። ይልቁኑ መስከረም 16 ለ17 አጥቢያ ጀምሮ ይለኮሳል እንጂ።) ለመስከረም 17 አጥቢያ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ ሁሉም ሰው ከየቤቱ ደቦቱ (ችቦውን) እየለኮሰ ‘እዮሃ ደመራ’ እያለ ወደ ደመራው ሥፍራ ይተማል። እንደየ ግለሰቡ ቤት እስከ ሦስት ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ሊጠይቅ ይችላል። የመስከረም እኩሌታ አረንጓዴያማ ውብ ማሳ ከየቤቱ ከሚወጡ የችቦ እሳት ነበልባል ብርሃን ይታጀባል። ከሌሎች አጎራባች የመንደር ደመራዎች ቀድሞ ለመለኮስ ጉጉቱ የትየለሌ ነው። ከቤት እስከ ደመራው ሥፍራ እስኪደርሱ ድረስ ሰዎችን፣ በረት ያሉ ከብቶቹንና የጓሮ አዝመራውን ጨምሮ ሕይወታዊያንን በሙሉ “እንጎረጎባህ፤ እንጎረጎባችሁ” ይባላል። የተጠያቂው ሰው ምላሽ ደግሞ “ዓመት ዓመቱን ያድርስህ” የሚል ይሆናል። ከደመራ ግጥም ተዘውታሪ ስንኞች መካከልም፡- “እዮሃ አበባዬ፣ መስከረም ጠባዬ፣ እዮሃ አረሬ አረሬ፣ መስቀል ጠባ ዛሬ፣ በሸዋ በትግሬ…” የሚለው ይጠቀሳል። ከደመራው ሥፍራ ስንደርስ የ’እንጎረጎባህ!’ ድምፆች ይበረታሉ። የ’ዓመቱን ያድርስህ’ መልስ ካልሆነም እኩይ አፀፋ ይኖራል። ሁሉም ከተሰባሰበ በኋላ ደመራን የሚያሞካሹና የአዲሱን ዓመት መልካምነት የሚመኙ ‘እዮሃ አበባዬ” ግጥሞች እየተደረደሩ ደመራው ሦስት ጊዜ እንቧለሌ ይዞራል። በዕድሜ ታላቅ እና የተከበረ ሰው በቅድሚያ ደመራውን ይለኩሳል። ቀጥሎ ሁሉም ወደ ደቦቱን(ችቦውን) ወደ ደመራው ውስጥ ያስገባል። ደመራውም ይቀጣጠላል። የእሳቱ ነበልባል በመስከረም የንጋት ውርጭና ብርድ ላይ ያይላል። ሁሉም በደመራው ዙሪያ ተኮልኩሎ የክረምት ወራት ትዝታ ይነሳል፤ ሹፈት፣ ቀልድና ቁምነገር በየፈርጁ ይሰለቃል። ሌሊቱ የአህያ ሆድ እስኪመስል ይቀጥላል። የተጣላም ይታረቃል። የደመራው አምድ (ምሰሶ) አወዳደቅ ለማየት ሁሉም በጉጉት ይጠብቃል። ምሰሶው ወደ ምሥራቅ ከወደቀ የጥጋብ ዓመት፤ ወደ ምዕራብ ከሆነ ግን የችጋር ዓመት ተደርጎ ይታመናል። ከደመራው ሁነቶች አንዱ ባህሉ የበቆሎ እሸት ናፍቆት ነው። የደመራው ምሰሶ ከወደቀ በኋላ በአቅራቢያ ካለ የበቆሎ ማሳ በቆሎ እሸት ይመጣል። በመስቀል ደመራ ፍም ተጠብሶ ይበላል። ባለበቆሎው ሰው ዓመታዊ ደንብ ስለሆነ የበቆሎ ማሳዬ ተጎዳብኝ ብሎ አይቆጣም። ከደመራው ዓመድ ግንባራችን ላይ መስቀለኛ ምልክት ማድረግ እና ‘የዛሬ ዓመት አድርሰኝ’ ስለት ይቀጥላል። ሰማዩ የአህያ ሆድ ሲመስል ልጆች በደቦ ወደ መንደር ለመንደር በመዞር ‘እንጎረጎባችሁ’ እንላለን። የቤቱ ባለቤትም በሳህን፣ ጣሳ ወይም ሌላ ዕቃ ጤፍ ዱቄት ይሰጣል። የሰበሰብነውን ዱቄት ይዘን ወደ ደመራው ሥፍራ እንመለሳለን። በደመራው ጉባዔ ተወስኖ ከዕድሩ ለተመረጠች ቀጭን እመቤት (ባለሙያ ሴት) ዱቄት ይሰጣትና በ17 ምሽት ለሚኖረው የእራት ሰዓት ዝግጅት በአነባበሮ መልክ ዱቄት አብኩታና ጋግራ ታቀርባለች። መስቀል የወል ክብረ በዓል ነው። የመስቀል ዕለት (መስከረም 17) በግ ይታረዳል። እህል ውሃ ቀርቦ የመንደሩ ሰው በጋራ ሲጫወት ይውላል፤ በሕብረት ይበላል። ለመስቀል የተጣላ ጎረቤት ይታረቃል። ልጆች በሕብረት ይቦርቃሉ። የመስቀል ትዝታ በእኛ መንደር ይናፈቃል። ሁሉም እንደየ ቀየው ትውፊት እና ልማድ ይህን ሁነት ይናፍቃል….!! ጊፋታ ጊፋታ/ ግፋታ ማለት ትርጉሙ በኩር ወይም ታላቅ ማለት ሲሆን በለኬላ ትርጓሜው መሻገር ማለት ነው፡፡ በወላይታ ብሔረሰብ አዲስ ዓመት አንድ ብሎ የሚጀመርበት የአዲስ ዓመት መግቢያና የብርሃን ጊዜ ማብሰሪያ ነው፡፡ ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሻገር የሚለውንም ይገልጻል፡፡ ጊፋታ የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ስያሜ ነው፡፡ በወላይታ ብሔረሰብ ዘንድ መስከረም ወር በገባ ከቀን 14 እስከ 20 መካከል የሚውለው እሑድ አዲሱን ዓመት የሚቀበሉበር ዕለት ይሆናል፡፡ በዓሉ የሚውልበት እሑድ ስሙም ‹‹ሹሃ ወጋ›› የእርድ እሑድ ይባላል፡፡ እሑድ የአዲስ ቀን ብሥራትም ነው፡፡ ቀጣዮቹ የሳምንቱ ቀናት የየራሳቸው ስያሜና አከባበር አላቸው። ለአብነት ‹‹ጋዜ ኦሩዋ›› ማንሳት ይቻላል። የአዲስ ዓመት አራተኛ ቀን ነው። የሰፈሩ ወጣቶች በየመንደሩ በታዋቂ የአገር ሽማግሌዎች ደጅ ተሰባስበው የግፋታ በዓል ባህላዊ ጨዋታ የሆነውን ጋዜ በጋራ ሆነው ‹‹ሀያያ ሌኬ›› እያሉ ትከሻ ለትከሻ ተቃቅፈው የሚጫወቱበትና ልጃገረዶችን ሎሚ በመለመን የሚፈልጓትን የሚመርጡበት ጨዋታ የሚጫወቱበት ቀን ነው፡፡ በዕለቱ ልጃገረዶች አንድ ላይ ሆነው በየቡድን ቁጭ ብለው ወንዴና ሴቴን ከበሮ እየመቱ ‹‹ወላወላሎሜ›› እያሉ የሚመርጡትን ወንድ ሎሚ በመስጠት የሚመርጡበት፣ እንዲሁም ሴቶች ለሚዜነትና ለጓደኝነት ከመረጧት ሴት ጋር በጥርስ አንድ ሎሚን ለሁለት የሚከፋፈሉበትና ስማቸው ሲጠራሩ ‹‹ሎሜ ሎሜ›› የሚባባሉበት ጨዋታ የሚጫወቱበት ዕለት ጋዜ ኦሩዋ ነው፡፡ ግፋታ ሲሸኝ ጥቅምት በገባ በመጀመሪያው ሳምንት ማክሰኞ ሆኖ የሽኝት በሬ ታርዶ ከተበላ በኋላ ቶክ ጤላ የተባለውን ምሽት በችቦ ያባርራሉ፡፡ ዜማ በተቀላቀለበት ጩኸት ችቦ ይዘው ‹‹ኦሎ ጎሮ ባ! ሳሮ ባዳ ሳሮ ያ!›› ይላሉ፡፡ ትርጓሜውም ጊፋታ በሰላም ሄደሽ በሰላም ነይ! ማለት ነው፡፡ ዮ …ማስቃላ በጋሞዎች ዘንድ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀው «ዮ ማስቃላ» የዘመን መለወጫ በዓል በመስከረም ወር አጋማሽ ላይ ቅበላው ተከብሮ በዚሁ ወር መጨረሻ «ዮ ማስቃላ» ሽኝት በዓል በድጋሚ በድምቀት ይከበራል። መስከረም ወር የመጀመሪያው ቀን በጋሞ ዞን ”ሂንግጫ” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ይህም አዲሱን ዓመት ለመቀበል ዝግጅት የሚደረግበት ቀን ነው። ጋሞዎች ዓመቱን ሙሉ ገንዘብ በመቆጠብ በዓሉን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ይደረጋል። ወንዶች ለበዓሉ የሚሆን ሠንጋ መግዣ፣ ለልጆች ልብስ እና ጌጣጌጥ ማሟያ፤ እናቶች ደግሞ ለቅቤ፣ ለቅመማቅመም፣ ለባህላዊ ምግቦች እና መጠጦች እህል መግዣ የሚሆን ገንዘብ ያጠራቅማሉ። በጋሞ ዞን የማስቃላ በዓል ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለእንሳስት እና ለአዕዋፋትም ጭምር ነው ተብሎ ይታመናል፤ በዕለቱ ምግብ ከሰው አልፎ ለእንሳስት እና ለአዕዋፍም ይትረፈረፋል። ለከብቶችም የግጦሸ መሬት በየአካባቢው ይከለላል። በተለያዩ አጋጣሚዎች የተጣሉ ታርቀው፣ የተራራቁ ዘመድ አዝማድ እና ወዳጆች ተሰባስበው በዓሉን በጋራ እንዲያከብሩ ማድረግ የጋሞ ማስቃላ በዓል መገለጫ ነው። በጋሞ ብሔረሰብ የሚከበረው የማስቃላ በዓል በሶፌ ሥርዓት የታጀበ ነው። የቀደመው ዓመት ማስቃላ በዓል ከተከበረ በኃላ የተጋቡ ሙሽሮች ከመስከረም አጋማሽ ጀምሮ ማምሻውን በአደባባይ ከመላው ሕብረተሰብ ጋር የሚቀላቀሉበት እና ሁለቱም ተጋቢ ቤተሰቦች አንድ ላይ ሆነው ደስታቸውን የሚገልፁበት ሥርዓት ነው። የመጨረሻው የማስቃላ ሽኝት በዓል ነው፤ ይህ ሥርዓት እንደየአባወራው አቅም በፈቀደ መጠን የሚፈፀም ነው። በዚህ ዕለት ሁሉም ያለ ፆታ ልዩነት በአደባባይ ላይ ወጥተው ያኑረን እስከ ወዲያኛው እንኖራለን እያሉ ይጨፍራሉ። ከዚህ በኋላ ለመጪው ዓመት በሰላም በጤና ያድርሰን ተባብለው ፈጣሪን በመማፀን ዝግጅቱ ይቋጫል። ያሆዴ መስቀላ የክረምቱ ወራት አልፈው መስኩ በልምላሜና በአደይ አበባ ሲያሸበርቅ በሃድያዎች ዘንድ ትልቅ ዝግጅት አለ - ያሆዴ መስቀላ። “ያሆዴ“ ማለት እንደ ብሔሩ የባህል ሽማግሌዎች ትርጓሜ እንኳን ደስ አላችሁ፤ የሚል የብስራት ትርጉም ያለው ሲሆን ”መስቀላ” ማለት ደግሞ ብርሃን ፈነጠቀ ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ያሆዴ መስቃላ ብርሃን ፈነጠቀ እንኳን ደስ አላችሁ የሚል ትርጉም አለው። በዓሉ በወርኃ መስከረም 16 የሚከበር ሲሆን ወሩ ብርሃን፣ ብሩህ ተስፋ፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ረድኤት፣ በረከት የሚሞላበት ተምሳሌት ወር ተደርጎ ይቆጠራል። የሃድያ አባቶች ”ከባለቤቱ የከረመች ነፍስ በያሆዴ መስቀላ ትነግሳለች“ የሚል ብሂል አላቸው። የሃድያ አባቶች እንደ ዘመን መለወጫ የመጀመሪያ ቀን አድርገው በመውሰድ ማንኛውንም ዓይነት ክስተት ከዚያ ጋር አያይዘው እንደሚቆጥሩ ይነገራል። በዓሉ ከመድረሱ በፊት ሁሉም የቤተሰብ አባላት በዓሉን ለማድመቅ የየራሳቸው ድርሻ አላቸው። በብሔሩ አባቶች አብሮነታቸውን ከሚያጠናክሩባቸው ማኅበራዊ እሴቶች መካከል አንዱ ቱታ/ሼማታ/ሲሆን ይህ ማለት በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተደራጀ ቋሚ የሆነ ከአራት እስከ ስምንት አባላትን የያዘና በሥጋ ቅርጫ የተደራጀ ማኅበር ነው። የዚህ ማኅበር አባላት ግንኙነት ያላቸው የሚተሳሰቡ የኢኮኖሚ አቅማቸውም ተቀራራቢነት ያለው ሲሆን በመቀናጀት የበዓሉ እለት ከመድረሱ በፊት በጋራ ገንዘብ ማስቀመጥ ይጀምራሉ፤ በበዓሉ ወቅትም ለእርድ የሚሆን በሬ መግዣ ገንዘብ እንዳይቸገሩና በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ ሕብረታቸው ትልቅ ሚና ይጫወታል። ከመጋቢት ወር ጀምሮ ለከብቶች የግጦሽ ሳር የሚሆን ቦታ ከልሎ በማስቀመጥ የበዓሉ ቀን ከብቶች ተለቀውበት እንዲጠግቡ የሚደረግ ሲሆን በአዲስ ዓመት መግቢያ እንኳን የሰው ልጅ እንሰሳትም ቢሆኑ መጥገብ እንዳለባቸው እንዲሁም የጥጋብ ዘመን እንዲሆን በብሔሩ በዓሉ ለሰው ብቻ ሳይሆን እንሰሳትም ሆዳቸው ሳይጎድል አዲሱን ዓመት መቀበል እንዳለባቸው በመታመኑ ልዩ ትኩረት ይሰጣቸዋል። ኢሬቻ ኢሬቻ ከመስከረም ደማቅ መልኮች አንዱ ነው። ኢሬቻ የዘመነ መፀው መጀመሪያ ሁነት ነው። የኢሬቻ ክብረ በዓል ኢሬቻ ቢራ (መልካ) በሐይቆች ወይም በወንዞች ዳር የሚከበር ነው። ከክረምት ወደ መፀው መሸጋገርን ምክንያት በማድረግ የሚከወን የምስጋና በዓል ነው። በኦሮሞ ዘንድ ለዘመናት የሚከበር እና ከገዳ ሥርዓት ጋር የተቆራኘ እንደሆነ ይነገራል። ኢሬቻ ከመስቀል በኋላ ይከበራል። በቢሾፍቱ ከተማ የሚከበረው የ'ሆራ አርሰዲ' እንዲሁም ‘ሆራ ፊንፊኔ’ ከፍተኛ ሕዝብ ቁጥር በታደመበት በድምቀት ይከበራል። በሌሎችም የኦሮሚያ አካባቢዎች በተለያዩ ክዋኔዎች እንዲሁ ይከበራል። ኢሬቻ ለፈጣሪ (ዋቃ) የክረምት ወቅትን በማሳለፉ፣ ወይንም ወደ አዲስ ዓመት በማሸጋገሩ የሚቀርብ ምስጋና ነው። ‹‹ዋቃ›› ፍጥረተ ዓለምን ያስገኘውና ሒደቱንም የሚያስተናብረው አንድ አምላክ ማለት ነው፡፡ ‹‹ኢሬቻ ሰላም ነው፣ ሰላም ጥልቅ ትርጉም አለው፣ ሰው ከሰው ጋር፣ ሰው ከራሱ ጋር፣ ሰው ከተፈጥሮ ጋርና ሰው ከፈጣሪው ጋር ሰላም ሊኖረው ይገባል፤›› የሚለው ጽንሰ ሐሳብ የክብረ በዓሉ ጭብጥ ነው፡፡ ለሕዝቡና ለአገሩ ምርቃትና መልካም ምኞት የሚገለጽበትም ነው-ኢሬቻ። ታዲያ ማንኛውም ሰው ወደ በዓሉ ሥፍራ ሲሄድ አለባበሱን ማሳመር ይጠበቅበታልኢሬቻ ከመስቀል በኋላ ይከበራል። በቢሾፍቱ ከተማ የሚከበረው የ'ሆራ አርሰዲ' እንዲሁም ‘ሆራ ፊንፊኔ’ ከፍተኛ ሕዝብ ቁጥር በታደመበት በድምቀት ይከበራል። በሌሎችም የኦሮሚያ አካባቢዎች በተለያዩ ክዋኔዎች እንዲሁ ይከበራል። ኢሬቻ እንደ ዕንቁጣጣሽ በመስከረም ጥባት ውሃ ጎድሎ፣ የተራራቀ ዘመድ አዝማድ የሚገናኝበት ነው። በተለያዩ ጸሐፍት እንደተጠቀሰው፣ ኢሬቻ አንድም ‘ዋቃ’ ከብርድና መብረቅ፣ ከጎርፍ፣ ከአውሎ ነፋስ እና መሰል የክረምት ተፈጥሯዊ ክስተቶች ጠብቆ ወደ ብራ እና ፀሐያማው የመፀው ወቅት በሰላም ስላሸጋገረ፣ አንድም በዋቃ ፈቃድ ዝናብ ዘንቦ፣ መሬቱ ረስርሶ፣ አዝመራው ለምልሞ፣ መልካም ፍሬ በመታየቱ፣ እሸት በመስጠቱ ስለማያልቀው ቸርነቱ ለማመስገን ነው። ከክረምቱ ጨለማ ወደ ብርሃን የማለፍ ብሥራት ነው ኢሬቻ። በሌላ በኩል ደግሞ መጪው አዲሱ ዓመት የተባረከና የተቀደሰ፣ የደስታና የብልፅግና፣ የተድላና ፍስሃ ይሆን ዘንድ መልካም ምኞትን የመግለጫ በዓልም ነው። በኢሬቻ ክዋኔ አባ ገዳዎችና የሕዝብ መሪዎች ይመርቃሉ። በኦሮሞ ሕዝብ ባህላዊ አለባበሱን በማጌጥ ወደ ክብረ-በዓሉ የሚያመሩ ኢሬቻ አክባሪዎች እርጥብ ሳር እና አደይ አበባን ይይዛሉ። ከኢሬቻ ክብረ-በዓል የምርቃት ስንኞች መዘን እንሰናበት። “… ለምድራችን ሰላም ስጥ! ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!)
ያሆዴ- የአዲስ ተስፋና ልምላሜ ምልክት
Sep 22, 2023 828
(በማሙሽ ጋረደው ከሆሳዕና) ያሆዴ የሃድያ ብሔር የአዲስ ዘመን መሸጋገሪያ በዓል ነው። በዓሉ ሲከበር ቂምና ቁርሾ ተወግዶ ያለፈው ዓመት መልካምና በጎ ያልሆነ ሁኔታ ታይቶ ለቀጣይ ስኬት አዲስ ተስፋና ልምላሜ ሰንቆ የሚሻገሩበት በዓልም እንደሆነ ይነገራል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የሃድያ ዞን አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ አቶ ታምሬ ኤርሚያስ እንዳሉት ሃድያ የራሱ የሆነ የጊዜ አቆጣጠር ባህል፤ ልማድ፤ ወግና ስርዓት አለው። ለዚህም እንደ ማሳያ በብሔሩ ዘንድ በከፍተኛ ድምቀት የሚከበረውን የያሆዴ ክብረ በዓል ለአብነት ጠቅሰዋል። በዓሉ የአዲስ ተስፋና ልምላሜ ምልክት ተደርጎ እንደሚወሰድ የተገለጸ ሲሆን በተለይም የሚመጣው ዘመን የስኬት እንዲሆን እያንዳንዱ ካለፈው ዓመት ስኬትና ውድቀት ልምድ እየቀመረ ሃገር ሰላም እንዲሆን ተመራርቀው በደስታ እየተበላ፤ እየተጠጣ የሚከበር በዓል መሆኑንም ተናግረዋል። በብሔሩ ዘንድ ልዩ ቦታ የሚሰጠው የያሆዴ ክብረ በዓል አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበትም ነው። በዓሉ ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ በተለያዩ ክዋኔዎች የሚከበር ሲሆን በዓሉ መቅረቡን ታዳጊ ልጆች በተለያዩ ገላጭ በሆኑ ድርጊቶች እንደሚያበስሩ አቶ ታምሬ ተናግረዋል። በተለይም ታዳጊዎቹ ያሆዴ መድረሱን ለማብሰር ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ እስከ ጳጉሜ መጨረሻ ድረስ በብሔሩ አጠራር ገምባቡያ ወይም (ዋሽንት) በመጠቀም የተለያዩ ጥዑመ ዜማዎችን በማሰማት በዓሉ መቅረቡን ያበስራሉ። በሃድያ ብሔር ዘንድ የአዲስ ዘመን ብስራት “ያሆዴ" የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰድ በዓል መሆኑንም አመልክተዋል። ይህም የሆነበት ምክንያት በመስከረም ሰውና እንስሳ ከዶፍ ዝናብ፣ ከውርጭ፣ ከጤዛና ከጭቃ፣ ከጉም፤ ከጭጋግና ጽልመት ነጻ ይሆናሉ። ምድሩ በሃምራዊ ቀለም ደምቆ ያሸበርቃል። ፀሐይ ሙሉ ገላዋን ገልጣ ጸዳሏን ትሰጣለች። በመሆኑም በስራ የደከመ ሰውነት ዘና፣ የታመመ ቀና ይልበታል፣ ልጅ አዋቂ የደስታ ነጋሪቱን ይጎስማል፣ የፍቅር ጽዋ ይጠጣል፣ የአእምሮ እርካታ ይነግሳል፣ በሁሉም ነገር ደስታ ይሰፍናል ወርሃ መስከረም በጥጋብና ደስታ ይጀመራል ። በዓሉ ከመግባቱ በፊት የራሱ የሆነ የሥራ ክፍፍል ኖሮት ቅድመ ዝግጅት የሚደረግበት መሆኑን ያነሱት ሃላፊው የቤተሰብ አባላት ሁሉም በየድርሻቸው ሃላፊነታቸውን እየተወጡ እንደሚጠብቁት ተናግረዋል። ለአብነትም ለበዓሉ መድመቅ በዓሉ ከመድረሱ ሦስትና አራት ወራት በፊት በአንድ ቤት ውስጥ የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት የሚወጡት ድርሻ አላቸው። የሃድያ አባቶች የያሆዴን የዘመን መለወጫ በዓል የሚያከብሩት በቅንጅት አማካኝነት ከአራት እስከ ስድስት ሰው በመሆን ተቀናጅተው ሰንጋ በመግዛት ነው። ለበዓሉ ሰንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ ማስቀመጥ የሚጀምሩትም ቀደም ብለው ነው ። እናቶች በዓሉ ከመቃረቡ ከሦስትና እና አራት ወራት በፊት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ለማጠራቀም በሚገቡት (ዊጆ) በተሰኘ ዕቁብ ቅቤ ማከማቸት ይጀምራሉ። በተጨማሪም ለስጋ መብያና ለአተካና መስሪያ የሚሆን እንሰት በመለየትና በመፋቅ፣ ቆጮ፣ ሜሬሮና፣ ቡላን ጨምሮ የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት የድርሻቸውን ይወጣሉ። የደረሱ ልጃገረዶች የቤቱን ወለል ቆፍረው ይደለድላሉ፣ የተለያዩ ውበት የሚሠጡ ቀለማትንና የተለያዩ ኖራዎችን በመጠቀም የቤቱን የውስጥና የውጭ ግርግዳን በመቀባት ያስውባሉ። ወጣቶች ከነሐሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚመርጡላቸውን ዛፍ፣ ግንድ ቆርጠው ለምግብ ማብሰያና ለደመራ የሚሆን ችቦ የማዘጋጀት ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይቆያሉ። ከመስከረም መግቢያ ጀምሮ ያሉ የቅዳሜ ገበያዎች ስያሜ (መቻል ሜራ ) የእብድ ገበያ በመባል ይጠራሉ።እነዚህ የግብይት ቀናት ከዚህ ቀደም እንደነበሩ የግብይት ቀናት በተረጋጋ መንገድ የሚተገበሩ ባለመሆኑና በጠዋት ቆሞ በጊዜ የሚበተን ገበያ በመሆኑ (መቻል ሜራ) የእብድ ገቢያ የሚል ስያሜ አሰጥቶታል ነው ያሉት አባቶች ሰንጋ ገዝተው ለመብላት ባደራጁት (ቱታ) ቅንጃ አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ ወደ መቻል ሜራ (እብድ ገበያ) በመሔድ የሚፈልጉትን ሰንጋ ገዝተው ይመለሳሉ። ገንዘብ ያላስቀመጡና በወቅቱ ማግኘት የማይችሉ አባወራዎች በዓሉን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተደስተው እንዲያሳልፉ ሌላኛው አማራጭ (ሃባ) በመባል የሚታወቅና ምንም ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች ለበዓሉ የሚሆን ሰንጋ በብድር የሚወስዱበት በብሔሩ ተወላጆች ዘንድ የኖረ የመተጋገዝና የመተሳሰብ እሴት አንዱ ነው። የሚፈልጉትን ሰንጋ ከመረጡ በኋላ እህል በሚደርስበት በታህሳስና በጥር ለመክፈል በዱቤ ይወስዳሉ። የበሬ ነጋዴውም ያለ ማንገራገር ሰንጋውን በመስጠት ወቅቱ ሲደርስ ገንዘቡን ለመውሰድ ተስማምቶ ይሰጥና ወቅቱን ጠብቆ ገንዘቡን ይወስዳል። በትውስት ተወስዶ ገንዘብ ያልከፈለ አባወራ ለቀጣይ የዘመን መለወጫ አይደርስም ተብሎ በብሔሩ ዘንድ ስለሚታመን በተስማሙበት ወቅት ገንዘቡን የመስጠት ግዴታቸው የተጠበቀ ነው። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ የመምሪያው ባለሙያ አቶ ይዲድያ ተስፋሁን እንዳሉት በዓሉ ያለው ለሌለው አካፍሎ በጋራ የሚበላበትና ወደ አዲስ ዘመን በጠንካራ አብሮነት የሚሻገሩበት ነው። በመሆኑም የያሆዴ በዓል በዜጎች መካከል ጠንካራ አንድነትና አብሮነትን መሰረት ያደረጉ ዕሴቶች ያሉበት መሆኑን አንስተው ለትውልድ ግንባታ የሚሆኑ ዕሴቶችን አጎልብቶ መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል ። ለበዓሉ ዋዜማ ከሚዘጋጁ ሁነቶች መካከል አተካና ልዩ ቦታ የሚሰጠው ነው። አተካና በተለይም ለዚህ በዓል ከዚህ ባሻገር ለትልልቅ እንግዶች ከሚዘጋጁ ምግቦች መካከል አንዱ ነው። አተካና ከወተት፣ ከቅቤ፣ አይብና ቡላ የሚዘጋጅና በበዓሉ የምግብ ፍላጎትን የሚከፍት ተበልቶ የማይጠገብ በእናቶች የሚዘጋጅ ጣፋጭ ምግብ ነው። የበዓሉ ዋዜማ አተካን ሂሞ (የአተካና ምሽት) የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን በዓሉን ለማክበር ከሩቅም ከቅርብም የተሰበሰበ ቤተሰብና እንግዶች በናፍቆት የሚመገቡት ምግብ ነው። በዚሁ ዕለት በአካባቢው ትልቅ የሚባል አባወራ (አዛውንት) ቤት ችቦ (ሳቴ ) ተዘጋጅቶ ማምሻውን አባቶች ወይም የሃገር ሽማግሌዎች የማቀጣጠያ (ጦምቦራ) ደመራ ማቀጣጠያ ይዘው ይወጣሉ። ከዚያም የአካባቢው ማህበረሰብም የሃገር ባህል ልብስ ለብሰው እንዲሁም ወጣቶች ተሰብስበው ያሆዴ ይጨፍራሉ። የሃገር ሽማግሌዎች ይመርቃሉ፤ ከዚያም የተዘጋጀውን ችቦ በእሳት ለኩሰው ያበራሉ። ይህም አዲስ ዘመን መግባቱን ማብሰርና ዓመቱ የብርሃን ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞት የሚገለፅበት ነው። ደመራው ከተቀጣጠለ በኃላ ወጣቶች ያሆዴ (ኦሌ) ጭፈራ ሲጫወቱ ያነጋሉ። ይህ ጭፈራ ከያሆዴ በዓል ውጭ አይጨፈርም። ወጣት ደመቀ አባቴ የሆሳዕና ከተማ ነዋሪ ሲሆን ስለ በዓሉ አስተያየቱን ሲሰጥ ''በአባቶች ደመራው ከተቀጣጠለ በኃላ እኛ ወጣቶች ያሆዴ ....ያህዴ....ሆያ ሆ... /ኦሌ/ ጭፈራ እየተጫወትን እናነጋለን፤'' ይህ ጭፈራ ከያሆዴ በዓል ውጭ ስለማይጨፈር በዓሉን ቀን በጉጉት እንደሚጠብቁት ተናግሯል። ተራርቀው የቆየ ወዳጅ ዘመድ ተሰብስቦ ያለምንም ልዩነት ችግርም ካለ በዕርቅና ሰላምን በማውረድ የሚመጣው ዘመን የልምላሜና የስኬት እንዲሆን ተመራርቀው የሚለያዩበት በዓል በመሆኑ በተስፋ የሚጠብቁት እንደሆነ ነው ወጣቱ የሚናገረው። የበዓሉ እለት ለዕርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኃላ የባህል ሽማግሌዎች (ጋቢማ ) ሥርዓት ያከናውናሉ። ክዋኔውም የበሬውን ሻኛ በለጋ ቅቤና በሠርዶ ሳር በመቀባትና ወተት በማፍሰስ ይከናወናል። ይህም በሚከናወንበት ወቅትም ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሃገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን በማለት (ፋቴ) ዳግም ምርቃት ፈጽመው በሬው ይጣልና የዕርድ ሥርዓት ይካሔዳል። በዕለቱም ከታረደው ሥጋ ቅምሻ በጋራ ይበሉና ቀሪውን ለማህበሩ (ለቱታ) አባላት ክፍፍል ይፈፀማል። ከእርድ ሥርዓቱ በኃላ በማግስቱ ልጆች ወደ ወላጆቻቸው ዘራሮ የሚባል አበባ ይዘው እየጨፈሩ ያስማሉ -ይመረቃሉ የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባባላሉ፤ ከስጋውም ፣ከቦርዴውም ፣ ከአተካናውም የሚመገቡበት ክዋኔ (ሚክራ) በመባል ይታወቃል። ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ስጋና (ዘራሮ) አደይ አበባ ጭምር ይዘው የሚሔዱበት እንዲሁም ያላገቡ ወጣቶች ለትዳር የሚሆናቸውን አጋር የሚፈልጉበትና የሚያጩበት ባህልም ያለው ነው ያሆዴ ክብረ በዓል። ከእርድ ስነ ስርዓቱ በኋላ ከሶስት ሳምንታት እስከ ወር ለሚሆን ጊዜ የመጠያየቂያና የመረዳጃ ወቅት ይሆናል። የያሆዴ በዓል ያሉ ዕሴቶች ለህዝብ ትስስር፣ ጠንካራ የስራ ባህልና ዘላቂ ሰላም ግንባታ ያላቸውን ሚና ለማላቅ በልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደምገባ የሚያነሱት በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የህዝብ ግንኙነትና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የአቶ ዳንኤል ገዴ በዚህ ላይ በአከባቢው ያሉ የማህበረሰብ ልምዶችና ወጎች ለትውልድ እንዲሸጋገሩ መስራትና የሃገር በቀል ዕውቀትን ማጠናከር እንደምገበባ ተናግረዋል። በዚህ ረገድ የዋቸሞ ዩኒቨረሲቲ የሃድያን ብሔር የዘመን አቆጣጠር ታሪክ : ባህልና ቋንቋ እንዲሁም ሌሎች ዕሴቶች ተሰንደው እንዲቀመጡና ለማስተማሪያነት እንዲውሉ ለማስቻል በጥናትና ምርምርና የተደገፈ ስራ በመስራት ላይ መሆኑን አመላክተዋል። በተጨማሪም ባህሉ ይበልጥ እንዲታወቅና በዩኔስኮ ተመዝግቦ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚገባውን ጥቅም እንዲያመጣና ከቱሪዝም አንጻር ሚናውን እንዲጫወት ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የመኔ ሸድዬ ባሮ - የጠንካራ የስራ ባህል፣ የአብሮነትና የሰላም ተምሳሌት
Sep 20, 2023 1402
በሽመልስ ጌታነህ (ኢዜአ) የመኔ ሸድዬ ባሮ የካፈቾ ብሄር ከአሮጌው ዘመን ወደ አዲሱ የሚሸጋገሩበት፣ የአዲስ ዘመን ብስራትና የዘመን መለወጫ በዓል ነው። በዓሉ የጠንካራ የስራ ባህል፣ የአብሮነትና የሰላም ተምሳሌት በዓል እንደሆነ ይነገርለታል። በዚህም የካፋ ብሄር ለዘመናት የገነባውና ጠንካራ የስራ ባህል፤ ተፈጥሮን የመጠበቅና የመንከባከብ እንዲሁም ከተለያዩ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ጋር ተቻችሎና ተፈቃቅሮ የሚኖር ሲሆን ቱባ ዕሴቱ ዛሬም ላለው ትውልድ መሰረት መሆኑን ያምኑበታል። የተለያዩ የታሪክ ድርሳናት እንደሚያሳዩት ከሆነ የካፋ ህዝብ ጠንካራ ንጉሳዊ ሥርዓት የነበረው፤ የታሪክና የቱባ ባህል ባለቤትም ነው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የታሪክ ባለሙያና የሀገር ሽማግሌ አቶ አሰፋ ገብረማሪያም የካፈቾ ብሄር ዘመን መለወጫ በሃገሬው አጠራር ''የመኔ ሸድዬ ባሮ'' በዓል የካፋ ህዝብ ከሚያከብራቸው በርካታ በዓላት ውስጥ ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው መሆኑን አፅንኦት ሰጥተው ይናገራሉ። በዓሉ ያለውን ግዝፈት ሲያመለክቱ በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በውጭ ፀሐፍት ጭምር “ታላቁ በዓል ወይም (ግሬት ፌስቲቫል)” ተብሎ እንደሚጠራም ተናግረዋል። በዓሉ ታሪካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ዳራ ያለው ሲሆን ከጥንት ካፋ ንጉስ ጀምሮ በየአመቱ በድምቀት የሚከበር በዓል እንደሆነም ጠቁመዋል። የካፋ ህዝብ ከ14ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ከጎሳ መሪነት አንስቶ ጠንካራ የመንግስት መዋቅር የነበረው ታላቅ ህዝብ እንደሆነ ያነሱት አቶ አሰፋ፣ በዚህም በዓሉ በዘመኑ የነበሩ መንግስታት በዓል እንደነበረም አብራርተዋል። ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም የሚገመገምበት ጥሩ የሠራና የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገበ የሚሸለምበትና ለበለጠ ሥልጣን የሚታጭበት፤ ሰነፉ ደግሞ የሚወቀስበትና ስልጣኑ የሚነጠቅበት ታላቅ በዓልም ነው ብለዋል። ይህም በብሄሩ ዘንድ ለዘመናት የተሻገረ የጠንካራ የሥራ ባህል ግንባታ መሰረት ሆኖ የቆየ መሆኑን አንስተዋል። ይህ ሁሉ ሲከናወን በማህበረሰባዊ የህግ ተገዥነት መሰረት መሆኑ የተለየ እንደሚያደርገው ገልጸው ከሁሉ በፊት ሰላምን በማስቀደም መንግስትንና ህግን ማክበር እንዲሁም ህግ የሚመራው ህዝብ የበላይ መሆኑን አመላካች ሥርዓት መሆኑን አንስተዋል። በዓሉ ከአዝመራ ጋር የተያያዘ የዘመን አቆጣጠርን ተከትሎ እንደሚከበርም የታሪክ ባለሙያው አቶ አሰፋ ይገልጻሉ። እንደ ታሪክ ተመራማሪው ገለጻ የካፋ ህዝብ አብዛኛው አርሶ አደር አልፎም አርብቶ አደር ሲሆን ለአዝመራ የተለየ ትኩረት ይሰጣል፤ በዓሉ ሊከበር 77 ቀናት ሲቀሩት ህዝቡ የአዲስ ዘመን መለወጫ ብሎ ሃምሌ አንድ አዝመራውን እንደሚጀምርም ጠቁመዋል። የአዝመራ ወቅት ሊገባደድ 25 ቀናት ሲቀሩት (ከሼ ዋጦ) ብሎ አዝመራውን ያጠናቅቃል። ወቅቱም ጨለማው አልፎ በብርሃን የሚተካበት፤ ክረምቱ ለበጋ ቦታውን የሚለቅበት በመሆኑ አዲስ አመት መድረሱን ያሳውቃል። ያን ጊዜ በጥንት የካፋ ምክርቤት ከሚገኙ ሰባት የሚክረቾ አባላት ውስጥ አንዱ የሆነው አዲዬ ራሾ ፤ የንጉሱ መቀመጫ በሆነው ቦንጌ ሸምበቶ በዓሉን ለማክበር ከየአቅጣጫው ለሚመጣው ህዝብ መንገዶችን በማፅዳት እና ለወንዞች ድልድይ በማበጀት በዓሉ መድረሱን ያበስራል። ያን ጊዜ በዓሉን ለማክበር ህዝብ ከያለበት አቅጣጫ ወደ ቦንጌ ሸምበቶ ይተማል። ህዝቡ በቦንጌ ሸምበቶ ከተሰበሰበ በኋላም ንጉሱ በተገኙበት የእያንዳንዱ ወራፌ ራሾ ሥራ ይገመገማል፤ ጥሩ ሥራ የሠራ ጠንካራ መሪ ይሸለማል፤ ለበለጠ ስልጣንም ይታጫል፤ ሀላፊነቱን በተገቢ ሁኔታ ያልተወጣው ደግሞ ይመከራል፣ ይወቀሳል አልፎም ስልጣኑን ይነጠቃል። ዛሬም ሀገራችን ይህ አይነቱን ጠንካራ የሥራ ባህል አብዝታ ትሻለች፤ እንዲህ አይነት ሀገር በቀል ዕውቀቶች ትውልዱን በጠንካራ ሥነ-ምግባርና የሥራ ባህል ለመገንባት ትልቅ ድርሻ አላቸው። በተጨማሪም በዓሉ ቅሬታዎችን ለመፍታትና ሰላምን ለማጠናከር ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ፤ ቂምና ጥላቻን ይዞ ወደ ንጉሱ ፊት መቆምም ይሁን ወደ አዲሱ ዓመት መሻገር ነውር ተደርጎ የሚወሰድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወደ በዓሉ ከመምጣቱ አስቀድሞም ይሁን በበዓሉ ወቅት የተጣላ ይታረቃል፤ ጥላቻም በፍቅር ይተካል ብለዋል የታሪክ ተመራማሪው። እንዲህ አይነቱ ሀገር በቀል ዕውቀት ጠንካራ ባህል ለመገንባት፤ ቅራኔዎችን በሰላም ለመፍታትና ማህበራዊ ግኑኝነቶችን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ ስላላቸው በትምህርት ሥርዓት ውስጥ አካቶ ማስተማርና ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ሲሉም ሃሳባቸውን አካፍለዋል። ሌላኛው የሀገር ሽማግሌና የካፋ፣ጫራ እና ናኦ የባህል ምክርቤት አባል አቶ ፀጋዬ ገብረማሪያም እንደሚሉት የካፋቾ ''የመኔ ሸድዬ ባሮ'' በዓል ማህበራዊ ግንኙነትን በማጠናከሩ ረገድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው በዓል ነው። ምክንያቱ ደግሞ፣ በዓሉን ለማክበር በአካባቢው ያሉ፣ በሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ እንዲሁም ባህር ማዶ የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆች የሚሰበሰቡበት ታላቅ በዓል ስለሆነ ነው ብለዋል። በዚህም የተራረቀ የሚገናኝበት፤ የተጠፋፋ የሚጠያየቅበት ሲሆን ህዝቡ በአንድ ላይ ተሰብስቦ በንጉሱ ተመርቆ፣ በልቶ ጠጥቶ እንዲሁም ተጫውቶ ወደ ቀጣዩ አመት በደስታና በታላቅ ተስፋ የሚሸጋገርበት እንደሆነም አብራርተዋል። ይህ ባህል በተለያዩ ምክንያቶች ከ120 ዓመታት በላይ ሳይከበር እንደቆየ የገለፁት አቶ ፀጋዬ ገብረማሪያም ዳግም መከበር ከጀመረበት ስምንት ዓመታት ወዲህ የነበረውን ታሪክና ባህል በሚያስቀጥል መልኩ በየዓመት በድምቀት እየተከበረ መሆኑንም አንስተዋል። ወጣቱ ትውልድ ባህሉንና ታሪኩን አውቆ እንዲኖርና እንዲያስቀጥል ግንዛቤ የመፍጠርና የማስተማር ሥራ በሰፊው እየተሠራ እንደሆነም ገልፀዋል። ከዚህ ባለፈም ባህሉንና ታሪኩን ለማስቀጠል የባህል ምክር ቤቱ የወረዳ የባህል ምክር ቤቶችን የማጠናከር፣ ታሪካዊ ቅርሶችን የመሰብሰብና የማደራጀት ሥራ እየሠራ ነውም ብለዋል። በዓሉ አንድነትን የሚያጠናክር፣ ጠንካራ የሥራ ባህልን የሚያበረታታ እና የተፈጥሮ ጥበቃን የሚያጠናክር በመሆኑ ከካፋ ብሔረሰብ በዓልነቱ ባለፈ የሀገርና የአለም ቅርስና ሀብት እንዲሆን ሰፊ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባም አቶ ፀጋዬ አሳስበዋል። የካፋቾ ዘመን መለወጫ በዓል (የመኔ ሸድዬ ባሮ) መሠረቱን ሳይለቅ ለትውልድ እንዲተላለፍ በዞን ደረጃ እየተሠራ መሆኑን የገለፁት የካፋ ዞን ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሃላፊ አቶ ተሾመ አምቦ ዘንድሮም ለዘጠነኛ ጊዜ በአደባባይ ለማክበር ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል። በዓሉ በሁሉም የካፋ ህዝብ በጋራ ያለምንም ልዩነት የሚከበር ታሪካዊ በዓል ሲሆን አለም አቀፋዊ እውቅና አግኝቶ በዩኔስኮ እንዲመዘገብ ለማስቻል ከተለያዩ ምሁራንና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመሆን የተለያዩ ጥናቶች እየተሠሩ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በበዓሉ ንጉሱ የተራቡትን የሚመግቡበት (ጮንጎ) የተሰኘ ስርዓት የሚፈፀምበትና የተጣሉ የሚታረቁበት ስርዓት እንደሚፈፀም የገለፁት አቶ ተሾመ አሁንም በዓሉ በየዓመቱ ሲከበር ይህ ሥርዓት ይከወናል ብለዋል። ቀጣይ ይህን በዓል በሰፊው አስተዋውቆ ወደ ቱሪዝም በማሳደግ ህዝቡ ከዘርፉ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችሉ ሥራዎች እንደተጀመሩም ሃላፊው ገልፀዋል። የዘንድሮው የ2016 ዓ.ም የካፊቾ ዘመን መለወጫ በዓል በቦንጋ ከተማ ከመስከረም 12 እስከ መስከረም 13/2016 ዓ.ም በፓናል ውይይትና በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበርም ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 5645
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 10621
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት። እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 4061
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል። “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 4917
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
መጣጥፍ
የዱርና የቤት እንስሳቱ ቤተሰባዊ ፍቅር
Dec 3, 2023 141
በፍሬዘር ጌታቸው (ወላይታ ሶዶ ኢዜአ) አብዛኛውን ጊዜ አንዳንድ የዱር እንስሳት ለሥጋቸው፣ ለቆዳቸው፣ ለጥርሳቸው ወዘተ እየተባለ እንደሚገደሉ የአደባባይ ምስጢር ነው። መንግሥት ይህንን ጥቃት ለመከላከል የተለያዩ የዱር እንስሳት ፓርኮችን በማቋቋም ጭምር የተለያዩ እርምጃዎችን ሲወስድ ይታያል። እርምጃው የዱር እንስሳቱን ከመጥፋት እንዲሁም መንግስት ዘርፉን በማስጎብኘት የሚያገኘውን ጥቅም ከመጨመር ባሻገር ሊኖረው የሚችለው ፋይዳ ብዙ ነው። የዱር እንስሳቱ ለአካባቢ ሥነ-ምህዳር የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ ሳይዘነጋ ማለት ነው። ሆኖም ግን አሁንም በሀገራችንም ሆነ በሌላው ዓለም የዱር እንስሳት በሰው ሰራሽም ሆነ የተፈጥሮ አደጋ ስጋት ላይ ናቸው። ለዛሬ የፅሁፌ ማጠንጠኛ የዱር እንስሳቱ ስጋትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሳይሆን እነሱን በማላመድ ያልተለመደ ተግባርን እየፈፀመ ባለ ግለሰብ ላይ ይሆናል። ግለሰቡ ወጣት በረከት ብርሃኑ ይባላል፤ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ ነው። ወጣት በረከት አዘወትረን የምንሰማውን 'እንኳን ሰው ወፍ ያለምዳሉ' የሚለውን ብሂል በሚያስረሳ መልኩ እሱ አባባሉን 'እንኳን ሰው አውሬ ያለምዳሉ' ወደሚለው ቀይሮታል ማለት ይቻላል። በረከት “በጎሪጥ የሚተያዩ የዱር እንስሳትን በፍቅር እንዲኖሩ ያደረገበትን ሁኔታ በርካቶች በግርምት ሲመለከቱት ይታያል። የሰው ልጆች በተፈጥሮ ክፉ ሆነው አይወለዱም ዳሩ ግን በህይወት አጋጣሚ ከሚቀስሙት ክፉ ባህሪ የሚማሩትና የሚዋሃዱበት እንጂ ይላል በረከት። ''አብሪያቸው ለመሆን በመወሰኔ እውነተኛ ፍቅርን ከዱር እንስሳቱ ተምሬያለሁ'' የሚለው ወጣት በረከት ከሰባት ዓመት በፊት የዱርና የቤት እንስሳትን በተለይም ሰው ለመቅረብ የሚፈራቸውን ጭምር እንደ ዘንዶ፣ ጅብ፣ ዝንጀሮ፣ አዞ፣ ጦጣ፣ አሳማ እንዲሁም ውሻና የመሳሰሉትን በማሰባሰብ በአንድ ላይ እንዲኖሩ እያደረገ በአንድ ላይ ማኖር እንደጀመረ ይናገራል። በዚህም ምክንያት ሰው ሰራሽ ሐይቅን በውስጡ የያዘ የወጣቶች መዝናኛ ፓርክ በወላይታ ሶዶ ከተማ ማቋቋሙን ገልጿል። የዱር እንስሳቱን ከአባያ ብላቴ እንዳመጣቸው የሚናገረው በረከት በይበልጥ ግን በመኪናና መሰል አደጋዎች የተጎዱ የዱር እንስሳትን ከወደቁበት በማንሳት እንዲያገግሙ ለማድረግ በሚያደርግላቸው የእንክብካቤ ቆይታ ታዲያ የዱር እንስሳቱ ከቤት እንስሳት ጋር አብረው የማደር፣ አብረው የመዋል፣ አብረው የመብላት፣ በአንድ ላይ የመጫወት ዕድሉን እንዳገኙ ነው ለኢዜአ የተናገረው። የቤትና የዱር እንስሳቱ ህብረትና አንድነት የሚያስቀና እንደሆነም ወጣት በረከት ገልጿል። ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ የዱር እንስሳት ሀብት እንዳለ የሚናገረው ወጣት በረከት በውስጡ ለተፈጥሮ ያለውን ፍቅር ወደ ስራ መቀየሩን ነው የገለፀው። ከሌሎች የዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ጋር በመሆን ስራውን ለመሥራት ወስነው በመግባታቸው የከተማው አስተዳደር የሥራ ቦታና መነሻ ካፒታል እንደረዳቸው ገልፆ በዚህም በመበረታታት ያልተለመደ የስራ ዘርፍ ለመፍጠር ወጥነው መጀመራቸውን ይናገራል። ስራውን ሲጀምር ቀላል ሁኔታ እንዳልገጠመው ያስታወሰው በረከት "ካባ ድንጋይ የሚፈነቀልበትን ስፍራ አልምቶና ችግኝ ተክሎ ወደ ዛፍ መቀየር እንዲሁም የሰው ሰራሽ ሐይቅ እንዲያመነጭ ማድረግ የማይቻል ይመስላል" ይላል። ቦታውን በባለሙያ በማስጠናትና ደባል አፈር ከሌላ ቦታ በማስመጣት ህልማቸውን እውን ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸውን አውስቶ ዓላማቸውን ለማሳካት የሄዱበት ርቀት ለሌሎች አስተማሪ መሆኑንም ይናገራል። ቦታውን አሁን ላይ የተለያዩ የዱርና የቤት እንስሳት በጋራ የሚኖሩበትና በርካታ የአገር ውስጥና ከሌላው ዓለም የሚመጡ ጎብኚዎች የሚዝናኑበትና የሚያርፉበት "ጁኒየር የወጣቶች መዝናኛ ፓርክ" መክፈት መቻላቸውን ነው የተናገረው። እንስሳቶች የሚሰጣቸውን ስያሜ ሳይሆን ተቀራርበው የሚኖሩበትን የፍቅር ህይወት ለማየት የሚመጣው ጎብኚ የቆይታ ጊዜ እንዲራዘም ማድረግ እንዳለበት በማመን የማረፊያ ቤቶች እና ተጨማሪ መዝናኛዎችን በማስፋፋት አሁን ላይ ጥሩ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ አብራርቷል። በዚህም ''በፓርኩ ግቢ ውስጥ የወላይታ ሶዶ ከተማን ገጽታ የሚያሳይ ባለ ሰባት በር መግቢያና መውጫ ያለው ሆቴልና የጀልባ መዝናኛ አገልግሎት ለተጠቃሚዎች በመስጠት የተሻለ ስራ በመስራት ላይ እንገኛለን'' ብሏል። ፓርኩን ለመጎብኘት ለሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ለአንድ ሰው 30 ብር፣ ለውጭ ዜጋ ደግሞ 100 ብር በማስከፈል አገልግሎት እየሰጡ ያነሳው ወጣቱ በአዘቦት ቀናት በቀን ከ400 በላይ ጎብኚ ፓርኩን እንደሚጎበኙ ፣ በሰንበት ቀናት እና በበዓላት ወቅት እስከ 1 ሺህ ድረስ ጎብኚዎች እንደሚመጡ ነው የተናገረው። ያንን ሁሉ አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ ባደረጉት ብርቱ ጥረት ከቤተሰብና በጥቂቱም ቢሆን ከመንግሥት ጥገኝነት መላቀቃቸውን የሚናገረው ወጣቱ በህይወታቸው ጥሩ ኑሮ መኖር ከመጀመራቸውም በዘለለ በፓርኩ ውስጥ ላለው የእንስሳት እንክብካቤና ጎብኚዎችን የማስተናገድ ስራን ለሚያሳልጡ 22 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር በመቻላቸውም ስኬታማ እንደሆኑም ያነሳል። "አሁን እንስሳቶቹ ቤተሰቦቼ ሆነዋል በአንድ ቅጥር ግቢ ውስጥ አብሬያቸው ውዬ ነው የማድረው ይላል። ስራ ሩቅ አይደለም አጠገባችን እንዲያውም እጃችን ላይ ነው ያለው የሚለው ወጣት በረከት ሆኖም ሌላ አካል መጥቶ እንዲሰጠን እንጠብቃለን፣ ይኸ አስተሳሰብ የእድገታችን ፀር ነው '' ሲልም አፅንኦት ሰጥቶታል። ኢትዮጵያ በዱር እንስሳት ሀብት በዓለም አቀፍ ደረጃ ስሟ የሚነሳ መሆኑን ጠቁሞ ሀብቱን ለማሳደግና ሳቢ በማድረግ ተደራሽነቱን ለማስፋት እንዲያመች የሎጅ ግንባታ ስራ እንቅስቃሴ ጀምሬያለሁ ባይ ነው። ፓርኩ ውስጥ 62 ምንጮች እንደሚገኙ የገለፀው ወጣት በረከት ማስፋፊያ ቦታ ቢሰጠው የተሻሉ ስራዎችን ለመስራት እቅድ እንዳለው ተናግሯል። በሰዎች ዓለም ውስጥ ገዢ ሀይል ፍቅር ሊሆን እንደሚገባ ፓርኩ ትልቅ የፍቅር ተምሳሌት ፓርክ ‼ ነው የሚሉት ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ አቶ ታዲዮስ ታንቱ ናቸው። ፓርኩ በሂደት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስሟ እንዲጠራ ጉልህ ሚና ይኖረዋል የሚል ተስፋ እንዳላቸው በመግለጽ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ትኩረትና ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። ፓርኩን ሲጎበኙ ያገኘናቸው የአዲስ አበባ ነዋሪው አቶ ለገሰ ቶማስ በበኩላቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየመነመነ ለመጣው የዱር እንስሳት ሀብት ማገገም የራሱን አስተዋጽኦ ሊያደርግ የሚችል ፓርክ መሆኑን ተናግረዋል። "ሁላችንም እንደዚሁ በእጃችን ያለውን ሀብት መጠቀም ካልጀመርን በቀር ሊለውጠን የሚመጣ ተዓምር አይኖርም'' ያሉት አስተያየት ሰጪው ከወጣት በረከት ሁሉም ብዙ ሊማር እንደሚገባም ጠቁመዋል።
“ዮ-ማስቃላ''- ሁሉም የሚደሰትበት በዓል
Sep 23, 2023 883
በሳሙኤል አየነው የሰላም፣ የአብሮነት፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የአንድነት ተምሳሌት የሆነው የጋሞ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል “ዮ-ማስቃላ” ከወርሃ መስከረም አጋማሽ ጀምሮ በተለያዩ ባህላዊ ሁነቶች በድምቀት ይከበራል ። በተለያየ ምክንያት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ተራርቀው የነበሩ ወገኖች ወደ የአካባቢያቸው በመመለስ ከቤተሰቦቻቸው ብሎም ከቀየው ህብረተሰብ ጋር አብረው የሚያከብሩት የዓመቱ ታላቅ በዓል ነው ። ታዲያ በዓሉን በድምቀት ለማክበር ወንዶች ሰንጋ በሬ ለመግዛት እንዲሁም ለትዳር አጋሮቻቸውና ለልጆቻቸው ልብስና ጌጣ ጌጥ የሚሆን ገንዘብ መቆጠብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ሴቶችም ለባህላዊ ምግቦች፣ ለቅመማ ቅመም፣ ለቅቤና ለባህላዊ መጠጦች እህል ግዥ የሚሆን ገንዘብ ዓመቱን ሙሉ ሲቆጥቡ ይከርማሉ። መስከረም ወር ከገባበት ዕለት አንስተው ወንዶችም ሆኑ ሴቶቹ በቆጠቡት ገንዘብ በየፊናቸው ለበዓሉ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን ማቅረብ ይጀምራሉ። ይህም የዝግጅት ጊዜ “እንግጫ” በመባል ይጥራል። በ”ዮ--ማስቃላ” ጊዜ አብሮነት እንጂ ግለኝነት የሚባል ነገር በጋሞዎች ዘንድ ፈጽሞ አይታሰብም፤ አብሮ እርድ ማካሄድ፣ አብሮ መመገብ፣ አብሮ መጠጣት፣ አብሮ መጫወት የጋሞዎች መገለጫ ነው። እንደ ሌሎቹ በዓላት ሁሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችም በዓሉን እንዴት እናሳልፍ የሚል ስጋት አያድርባቸውም። ምክንያቱም የሌለውም ካለው ጋር አብሮ የሚቋደስበት፣ የሚደሰትበት፣ የሚተሳሰብበትና የሰብአዊነት ልክ የሚንጸባረቅበት ልዩ ድባብ ያለው በዓል ነውና ዮ-ማስቃላ ። የጋሞ የሀገር ሽማግሌ አቶ አመሌ አልቶ ስለ “ዮ--ማስቃላ” በዓል በትንሹ እንዲያወጉን ጠይቀናቸው በዓሉ ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን እንስሳትና አዕዋፋት ሁሉ የሚደሰቱበት እንደሆነ ነግረውናል። በአካባቢው ቋንቋ ተፈጥሮ ሁሉ በዓሉን በደስታ እንደሚያሳልፍ ለመግለጽ “ካፎስ ካናስ ማስቃላ” በማለት የሚገለጽ ስሆን “ለሰው ብቻ ሳይሆን ለእንስሳትም መስቀል ነው” እንደማለት ነው ብለዋል። በዓሉ ከመድረሱ ከሶስት ወራት አስቀድሞ በየአካባቢው ለእንስሳት የግጦሽ ሥፍራ ተከልሎ የሚዘጋጅ ሲሆን ችቦው በሚለኮስበት በደመራው ዕለት የቤት እንስሳት በሙሉ በዚያው የሚሰማሩ ይሆናል። ዓመቱን ሙሉ ሲያርሱ የነበሩ የእርሻ መሣሪያዎችም በበዓሉ ጊዜ ታጥበውና በቅቤ ታሽተው በክብር ይቀመጣሉ። ክብር ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለእንስሳትና ለእርሻ መሣሪያዎችም ይሰጣል። በባህሉ መሠረት ችቦ በሚወጣበት ሰዓት አባት የራሱን ችቦ ለኩሶ የቤቱን ምሰሶ፣ የከብቶችን ጋጣና የበር ጉበኖችን ግራና ቀኝ በችቦው ጫፍ በማነካካት ወደ ውጭ ካወጣ በኋላ ወንድ ልጆች የየራሳቸውን ችቦ ተራ በተራ እየለኮሱ አባታቸውን ተከትለው “ዮ---ማስቃላ” እያሉ ወደ ደመራ ቦታ ያመራሉ። ከዚያም አባት በቅድሚያ ችቦውን ከለኮሰ በኋላ ልጆች ደግሞ ተከትለው ደመራውን ይለኩሳሉ። ከዚህ ፕሮግራም መልስ ወደ ቤት ተመልሰው የተዘጋጀውን ገንፎ በአንድ ወጭት ላይ “ዮ--ማስቃላ”እያሉ ሁሉም የቤተሰብ አባላት፣ ዘመድ አዝማድና ጎረቤት ተሰባስበው በጋራ ይመገባሉ። በ”ዮ--ማስቃላ” በዓል በዋናነት እርድ የሚከወን ሲሆን ቁርጥ፣ ጎረድ ጎረድ፣ ክትፎና የወጣ ወጥ ዓይነቶች ተሠርተው ለምግብነት ይቀርባሉ። ከባህላዊ ምግቦች ደግሞ የገብስ ቅንጬ፣ የቆጮና ገብስ ውህድ ቂጣ፣ የቡላ ፍርፍር፣ ሀረግ ቦዬ፣ እንዲሁም ከመጠጥ አይነቶች ደግሞ ቦርዴ፣ ጠላ፣ የማርና የቦርዴ ጠላ ውህድና ሌሎች ተወዳጅ ምግቦችና መጠጦች ይዘጋጃሉ። በ”ዮ--ማስቃላ” በዓል ዕለት የሚቀራረቡ ጎረቤታሞች በጋራ ሆነው አማካይ በሆነ ሥፍራ ላይ የእርድ ሥነሥርዓት ያከናውናሉ። የእርድ ሥነ-ሥርአቱም በደመራው ዕለትና ማግስት እንደ ህብረተሰቡ ይሁንታ የሚፈጸም ይሆናል። ከማግስቱ ጀምሮ የተዘጋጀውን ሥጋ በጋራ እየበሉና እየጠጡ የበዓሉን ድባብ የሚያስቀጥሉ ሲሆን “ዱንግዛ” በተሰኘው የጋሞ ባህላዊ ጥበብ ልብስ ደምቀው በጌጣጌጥ አሸብርቀው ሁሉም በየአደባባዩ በባህላዊ ጫዋታዎች እየተደሰተ በዓሉን ያከብራል። ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነትና አብሮነት ካለ በአዲሱ ዓመት ምድሪቱ ተገቢውን ምርት እንደምትሰጥ ሁሉም ሰው በተሰማራበት መስክ ውጤታማ እንደሚሆን ይታመናል። ከዚም የተነሳ በአሮጌው ዓመት ሃዘን ላይ የነበሩ ወገኖች ሙሉ በሙሉ ሀዘናቸውን በመተው በአዲስ መንፈስ ወደ መደበኛው ህይወት ይመለሳሉ። የተጣሉ ወገኖች ቂም ይዘው አዲስ ዓመትን መሻገር በጋሞዎች ዘንድ ነውር በመሆኑ በባህላዊ ሸንጎ ሥርአት /ዱቡሻ/ በጋሞ አባቶች አሸማጋይነት እርስ በርስ ተነጋግረው በመታረቅ አዲሱን ዓመት በጋራ ያበስሩታል። በሌላ መንገድ “ዮ..ማስቃላ” በዓል ተጠብቆ ወጣቶች የሚተጫጩበት፣ የተጫጩት ደግሞ ጋብቻ የሚከውኑበት እንዲሁም ያገቡት በየገበያው ዕለት “ሶፌ” የሚባል ሥነ-ሥርዓት በማከናወን በማህበራዊ ህይወት ማህበረሰቡን በይፋ የሚቀላቀሉበት መሆኑን ጋሽ አመሌ አውግተውናል። ጋሞዎች ከሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች ጋር በመሆን በአብሮነት ለሁለት ሳምንታት በደስታ ካሳለፉ በኋላ ወደ ግብርና ሥራቸው በመመለስ ቀደም ሲል በክብር ያስቀመጧቸውን የእርሻ መሣሪያዎች በማንሳት ወደ እርሻ ሥራ ይገባሉ። እስከ ታህሳስ ወር መውጫ ድረስ የበዓሉ ድባብ ሳይጠፋ ይቆይና በመጨረሻም የመሰናበቻ ድግስ ወይም “ጮዬ ማስቃላ” በማዘጋጀት በህብረት ከተመገቡና ከጠጡ በኋላ የዓመት ሰው ይበለን፣ ዓመቱ የሰላም፣ የጤና፣ የበረከት ይሁን በማለት በመመራረቅ “ዮ--ማስቃላ”ን ይሸኛሉ። በዓሉ የህዝቡን ሰላም ፣አንድነትና አብሮነት የሚያንጸባርቅ ልዩ በዓል ነው በማለት የጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ አቶ ሞናዬ ሞሶሌ የጋሞ የሀገር ሽማግሌ የሆኑት የአቶ አመሌ አልቶን ሃሳብ ይጋራሉ። ባህላዊ እሴቱ ከትውልድ ወደ ትውልድ ተጠብቆ እንዲቆይ “ዮ--ማስቃላ” ትልቅ ድርሻ አለው። የባህል እሴቶች ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፉ በጥናትና ምርምር በማስገፍና የቋንቋና ባህል አውደ ጥናት በየዓመቱ እየተደረገ እንደሆነም ነግረውናል። አባቶች በልዩነት ውስጥ ያለንን አንድነት እንዳቆዩልን ሁሉ ወጣቶችም ኢትዮጵያዊ ለዛ ያላቸው የጋራ እሴቶች ሳይበረዙና ሳይከለሱ ጠብቀው ለትውልድ የማስተላለፍ ሃላፊነት አለባቸው የሚለውን የንግግራቸው ማሳረጊያ አድርገዋል።