ስፖርት - ኢዜአ አማርኛ
ስፖርት
በሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ ሁለት የሚደረጉ ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Jul 13, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ። ናይጄሪያ ከአልጄሪያ በላርቢ ዛውሊ ስታዲየም፣ ቱኒዚያ ከቦትስዋና በፔሬ-ጄጎ ስታዲየም በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። የዘጠኝ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ናይጄሪያ በስድስት ነጥብ ወደ ሩብ ፍጻሜ መግባቷን ማረጋገጧ ይታወሳል። ማሸነፍ ወይም አቻ መውጣት የምድቡ መሪ ሆና እንድታጠናቅቅ ያስችላታል። በአራት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው አልጄሪያ ማሸነፍ በቀጥታ ወደ ሩብ ፍጻሜው ያስገባታል። ተሸንፋም ወይም አቻ ወጥታ ሁለተኛ ሆና ወይንም ምርጥ ሶስተኛ ሆና ልታልፍ ትችላለች። በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ቱኒዚያ ወደ ሩብ ፍጻሜው ለመግባት ማሸነፍ ግድ ይላታል። ለሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አራት ነጥብ በናይጄሪያና አልጄሪያ ጨዋታ ውጤት ላይ ተመስርታ ሁለተኛ ወይም ምርጥ ሶስተኛ ሆና ልታልፍ ትችላለች። ሁለት ሽንፈት አስተናግዳ ያለ ምንም ነጥብ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን የያዘችው ቦትስዋና ማሸነፍ ምርጥ ሶስተኛ ሆና እንድታልፍ የሚያደርግ እድል ሊሰጣት ይችላል።
የአውሮፓ ኃያላኑ ቼልሲ እና ፒኤስጂ የክለቦች ዓለም ዋንጫን ለማንሳት ይፋለማሉ
Jul 13, 2025 61
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ ቼልሲ እና ፒኤስጂ ዛሬ የፍጻሜ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፍጻሜው ጨዋታ ላይ ይታደማሉ። የፍጻሜው ጨዋታ 82 ሺህ 500 ተመልካች በሚያስተናግደው ሜት ላይፍ ስታዲየም ምሽት 4 ሰዓት ላይ ይካሄዳል። ቼልሲ በግማሽ ፍጻሜው የብራዚሉን ፍሉሜኔንሴን 2 ለ 0 አሸንፏል። ፒኤስጂ ሪያል ማድሪድ 4 ለ 0 በመርታት ለፍጻሜው አልፏል። ቼልሲ እና ፒኤስጂ ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 10 የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ፒኤስጂ 5 ጊዜ ሲያሸንፍ ቼልሲ 2 ጊዜ አሸንፏል። 3 ጊዜ አቻ ወጥተዋል። ሁለቱ ቡድኖች ስምንት ጊዜ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተገናኝተው ፒኤስጂ 3 ጊዜ ድል ሲቀናው ቼልሲ 2 ጊዜ አሸንፏል። በቀሪዎቹ ሶስት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርተዋል። አስደናቂው ፒኤስጂ የአሸናፊነት ስነ ልቦናው፣ የተከላከይ መስመሩ ጥንካሬ፣ የአማካይ ክፍሉ ኳስ የመቆጣጠር ብቃት እና ፈጣን የማጥቃት እንቅስቃሴው ከብዙዎች አድናቆት እያስቸረው ነው። የፓሪሱ ክለብ በክለቦች ዓለም ዋንጫ እስከ አሁን ባደረጋቸው ስድስት ጨዋታዎች አምስት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። 16 ግቦችን ሲያስቆጥር ያስተናገደው አንድ ግብ ብቻ ነው። ቡድኑ ከስድስቱ ጨዋታዎች በአምስቱ ግብ አልተቆጠረበትም። የተከላካይ መስመር ክፍሉ ተጋላጭነት፣ የትኩረት ማጣት አጋጣሚዎች እና ግብ የመፍጠር ኃላፊነት በተወሰኑ ተጫዋቾች ላይ የተንጠለጠለ መሆኑ ፒኤስጂ እንደ ድክመት ሊነሱበት የሚችሉ ጉዳዮች ናቸው። ተጋጣሚው ቼልሲ በወጣቶች እና የመጫወት ረሃብ ባላቸው ባለክህሎቶች የተሞላ ነው። የአማካይ ክፍሉ ጥንካሬ እና ሚዛን፣ የታክቲክ ተለዋዋጭነት እና የታክቲክ ተገዢነት እንዲሁም የማጥቃት አቅም የምዕራብ ለንደኑ ቡድን የጥንካሬ መገለጫዎች ናቸው። ቡድኑ በውድድሩ ባደረጋቸው ስድስት ጨዋታዎች አምስት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏልክ። 14 ግቦችን ሲያስቆጥር 5 ግቦች ተቆጥረውበታል። የተከላካይ ክፍሉ የአደጋ ተጋላጭነት፣ ልምድ ማነስ እና የጎል ማስቆጠር ያሉ ችግሮች አንድ ድክመት ይነሱበታል። ፒኤስጂ ከፈረንሳይ ሊግ 1፣ የፈረንሳይ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ እና የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ድሉ በኋላ አራተኛውን ዋንጫ ለማንሳት ይፋለማል። ቼልሲ ከአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ድሉ ላይ የክለቦች የዓለም ዋንጫን ለመጨመር ይጫወታል። ፒኤስጂ ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ ግምቱን ቢውሰድም ዋንጫ ካየ ወደ ኋላ ከማይለው ቼልሲ ጠንካራ ፈተና ይጠብቀዋል። የኢራን እና አውስትራሊያ ጥምር ዜግነት ያላቸው የ47 ዓመቱ አሊሬዛ ፋግሃኒ ተጠባቂውን የፍጻሜ ጨዋታው በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፍጻሜውን ጨዋታ በሜትላይፍ ስታዲየም ተገኝተው እንደሚከታተሉ ተረጋግጧል። የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ለውድድሩ ተሳታፊዎች በአጠቃይ የአንድ ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽልማት አዘጋጅቷል። ውድድሩን የሚያሸንፈው ቡድን የ40 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽልማት ያገኛል። ለፍጻሜ ያለፉ ቡድኖች ለፍጻሜ በማለፋቸው ብቻ 30 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይበረከትላቸዋል።
ሞሮኮ እና ዛምቢያ ለሩብ ፍጻሜ አለፉ
Jul 13, 2025 55
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ማምሻውን ተደርገዋል። በፕሪንስ ሙላይ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አዘጋጇ ሞሮኮ ሴኔጋልን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ያሲን ምራቤት በመጀመሪያ አጋማሽ ጭማሪ ደቂቃዎች ላይ በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠረችው ግብ ቡድኑን ባለድል አድርጋለች። ሞሮኮ በሰባት ነጥብ የምድቡ መሪ ሆና በማጠናቀቅ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች። በዚሁ ምድብ ማምሻውን በተመሳሳይ ሰዓት በኤል ባቺር ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ዛምቢያ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን 1 ለ 0 ረታለች። ራቼል ኩንዳናንጂ የማሸነፊያውን ጎል በ9ኛው ደቂቃ አስቆጥራለች። የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የአጥቂ መስመር ተሰላፊ ፋሎኔ ፓምባኒ በ69ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብታለች። ውጤቱን ተከትሎ ዛምቢያ በተመሳሳይ ሰባት ነጥብ በሞሮኮ በግብ ክፍያ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ሩብ ፍጻሜ ገብታለች። በምድቡ ሶስቱንም ጨዋታ የተሸነፈችው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ከውድድሩ የተሰናበተች የመጀመሪያ ሀገርም ሆናለች። በምድብ አንድ በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ይዛ የጨረሰችው ሴኔጋል ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ ለማለፍ የሌሎች ምድብ ውጤቶችን ትጠብቃለች። ናይጄሪያ ሩብ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያ ሀገር መሆኗ ይታወቃል።
የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ
Jul 12, 2025 84
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ ሶስተኛ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ። ከምሽቱ 4 ላይ አዘጋጇ ሞሮኮ ከሴኔጋል በፕሪስን ሙላይ አብደላ ስታዲየም ይጫወታሉ። በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ዛምቢያ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኤል ባቺር ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ሞሮኮ አራት ነጥብ በመያዝ ምድቡን በአራት ነጥብ እየመራች ትገኛለች። ሴኔጋል በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛለች። አዘጋጅ ሀገር ሞሮኮ ማሸነፍ ወይም አቻ መውጣት ወደ ሩብ ፍጻሜው ያሳልፋታል። ተሸንፋም ጥሩ ሶስተኛ ሆኖ የማለፍ እድል አላት። ሴኔጋል ካሸነፈች በቀጥታ ሩብ ፍጻሜውን ትቀላቀላለች። አቻ መውጣት ወይም መሸነፍ ሁለተኛ አሊያም ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ እንድታልፍ ሊያደርጋት ይችላል። ዛምቢያ በምድቡ አራት ነጥብ በመሰብሰብ ተመሳሳይ ነጥብ ባላት አዘጋጇ ሞሮኮ በግብ ክፍያ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። ማሸነፍ ዛምቢያ የማንንም ውጤት ሳትጠብቅ ወደ ሩብ ፍጻሜ እንድትገባ ያስችላታል። ተሸንፋ ወይም አቻ ወጥታ በሂሳባዊ ስሌት ቀጣዩን ዙር የመቀላቀል እድል ልታገኝ ትችላለች። ሁለት ሽንፈት ያስተናገደችው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛለች። ማሸነፍ የኮንጎን ምርጥ ሶስተኛ ሆና የማለፍ እድሏን ሊያለመልመው ይችላል።
ታንዛንያ እና ደቡብ አፍሪካ ነጥብ ተጋርተዋል
Jul 12, 2025 83
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት መርሃ ግብር ታንዛንያ እና ደቡብ አፍሪካ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ትናንት ማምሻውን በሆነር ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አጥቂዋ ኦፓ ክሌመንት በ24ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠረችው ግብ ታንዛንያ መሪ ሆናለች። የተከላካይ መስመር ተሰላፊዋ ባምባናኒ ምባኔ በ70ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ላይ ያሳረፈችው ጎል ደቡብ አፍሪካን አቻ አድርጓል። የታንዛንያዋ ኤልሳቤት ጆን ቼንጌ በ84ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ሜዳ ተሰናብታለች። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ደቡብ አፍሪካ በአራት ነጥብ የምድቡን መሪነት ከማሊ ተረክባለች። ታንዛንያ በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዚሁ ምድብ ትናንት በተደረገ ጨዋታ ጋና እና ማሊ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ደቡብ አፍሪካ ከማሊ፣ ጋና ከታንዛንያ የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም የመጨረሻ የምድብ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ጋና እና ማሊ ነጥብ ተጋሩ
Jul 11, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት ጨዋታ ጋና እና ማሊ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ማምሻውን በቤርካኔ ሙኒሲፓል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የአማካይ መስመር ተሰላፊዋ አሊስ ኩሲ በስድስተኛው ደቂቃ ያስቆጠረችው ግብ ጋናን መሪ መሆን ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ አጥቂዋ አይሳታ ትራኦሬ በ52ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፈችው ግብ ማሊን አቻ አድርጋለች። በጨዋታው ብልጫ ወስዳ የተጫወተችው ጋና ያገኘቻቸውን ግልጽ የግብ እድሎች አልተጠቀመችበትም። ውጤቱን ተከትሎ ማሊ ነጥቧን ወደ አራት ከፍ በማድረግ በምድብ መሪነቷ ቀጥላለች። ጋና በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ዙር የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ
Jul 11, 2025 99
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የሰባተኛ ቀን ውሎ የምድብ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምዕራብ አፍሪካውያኑ ጋና እና ማሊ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ በቤርካኔ ሙኒሲፓል ስታዲየም ይጫወታሉ። ጋና በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በደቡብ አፍሪካ የ2 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። ማሊ በበኩሏ ታንዛንያን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ጋና በውድድሩ ለመቆየት የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ ይኖርባታል። በአንጻሩ ማሊ ድል ከቀናት ሩብ ፍጻሜውን ትቀላቀላለች። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም አምስት ጊዜ እርስ በእርስ ተጫውተው ጋና ሶስት ጊዜ ስታሸንፍ ማሊ አንድ ጊዜ ድል ቀንቷታል። በቀሪው ጨዋታ ነጥብ ተጋርተዋል። በጨዋታዎቹ ጋና 15 ግቦችን ከመረብ ጋር ስታገናኝ ማሊ 12 ግቦችን አስቆጥራለች። ባላቸው የእርስ በእርስ ታሪክ ጋና የተሻለ የማሸነፍ ግምት ብታገኝም በጥሩ ወቅታዊ ብቃት ላይ የምትገኘው ማሊ ተጋጣሚዋን የመፈተን አቅም አላት። በዚሁ ምድብ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ታንዛንያ ከደቡብ አፍሪካ በሆነር ስታዲየም ይጫወታሉ። ደቡብ አፍሪካ በሶስት ነጥብ ምድቡን እየመራች ነው። ታንዛንያ ያለ ምንም ነጥብ በአንድ የግብ እዳ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት ደቡብ አፍሪካ ካሸነፈች ሩብ ፍጻሜ ትገባለች። ታንዛንያ በውድድሩ የመጀመሪያ ድሏን ለማስመዝገብ ጠንካራ ተጋጣሚዋን መርታት ይኖርባታል። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ ተገናኝተው ደቡብ አፍሪካ ሶስት ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዛለች። በቀሪው ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። ደቡብ አፍሪካ በጨዋታዎቹ ስምንት ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ታንዛንያ ሶስት ግቦችን አስቆጥራለች።
ናይጄሪያ ለሩብ ፍጻሜ አለፈች
Jul 11, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት መርሃ ግብር ናይጄሪያ ቦትስዋናን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በላርቢ ዛውሊ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አጥቂዋ ቺንዌንዱ ለሄዙ በ89ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥራለች። ናይጄሪያ በጨዋታው ባደረገችው የመጀመሪያ ኢላማውን የጠበቀ የግብ ሙከራ ነው ጎል ማስቆጠር የቻለችው። በጨዋታው ጠንካራ ፉክክር የተደረገ ሲሆን ቦትስዋና የዘጠኝ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ናይጄሪያን ፈትናታለች። ውጤቱን ተከትሎ ናይጄሪያ በስድስት ነጥብ አንድ ጨዋታ እየቀራት ለሩብ ፍጻሜ አልፋለች። ቡድኑ ወደ ቀጣዩ ዙር ቢሸጋገርም የማጥቃት ድክመቱን ማረም እንደሚጠበቅበት በመገለጽ ላይ ይገኛል። ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ቦትስዋና ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛለች። በዚሁ ምድብ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ቱኒዚያ እና አልጄሪያ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል። አልጄሪያ በአራት ነጥብ ሁለተኛ እና ቱኒዚያ በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። ናይጄሪያን ከአልጄሪያ፣ ቱኒዚያ ከቦትስዋና የፊታችን እሁድ ሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ.ም የሚደረጉ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዎች ናቸው። በሶስት ምድብ ተከፍሎ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው 13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ከየምድቡ አንደኛ እና ሁለተኛ የሚወጡ ሀገራት ለሩብ ፍጻሜ ያልፋሉ። ከምድቦቹ ምርጥ ሶስተኛ ሆነው የሚያጠናቅቁ ተጨማሪ ሁለት ሀገራት ሩብ ፍጻሜውን ይቀላቀላሉ።
ቱኒዚያ እና አልጄሪያ ነጥብ ተጋርተዋል
Jul 10, 2025 96
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት ጨዋታ ቱኒዚያ እና አልጄሪያ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ጨዋታው ማምሻውን በበፔሬ ጄጎ ስታዲየም ተካሄዷል። አልጄሪያ በኳስ ቁጥጥር እና የግብ እድል በመፍጠር የነበራትን ብልጫ ወደ ውጤት መቀየር አልቻለችም። መርሃ ግብሩ በአፍሪካ ዋንጫው ምንም ግብ ያልተቆጠረበት የመጀመሪያው ጨዋታ ሆኗል። ውጤቱን ተከትሎ አልጄሪያ በአራት ነጥብ ምድቡን እየመራች ነው። ቱኒዚያ በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዛለች። በምድብ ሶስት ቦትስዋና ከናይጄሪያ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በላርቢ ዛውሊ ስታዲየም ይጫወታሉ። የዘጠኝ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ናይጄሪያ በሶስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። ካሸነፈች የምድቡን መሪነት ከአልጄሪያ ትረክባለች። ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ የያዘችው ቦትስዋና የመጀመሪያ ድሏን ለማስመዝገብ ትጫወታለች።
በሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ
Jul 10, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት ሁለተኛ መርሃ ግብር ዛሬ ይደረጋል። ቱኒዚያ እና አልጄሪያ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ በፔሬ ጄጎ ስታዲየም ይጫወታሉ። ቱኒዚያ በመጀመሪያ ጨዋታዋ በናይጄሪያ 3 ለ 0 ስትሸነፍ አልጄሪያ ቦትስዋናን 1 ለ 0 ረታለች። ማሸነፍ ቱኒዚያ በውድድሩ የመቆየት እድሏን እንዲሰፋ ያደርጋል። አልጄሪያ ካሸነፈች ሩብ ፍጻሜ ትገባለች። የሰሜን አፍሪካ ሀገራቱ ከዚህ ቀደም 11 ጊዜ ተገናኝተው አልጄሪያ 6 ጊዜ በማሸነፍ ብልጫውን ወስዳለች። ቱኒዚያ 2 ጊዜ ስታሸንፍ 3 ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። አልጄሪያ በጨዋታዎቹ 21 ግቦችን ስታስቆጥር ቱኒዚያ 14 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፋለች። የምድብ ሁለት ሌላኛው ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በላርቢ ዛውሊ ስታዲየም ናይጄሪያ እና ቦትስዋናን ያገናኛል። የዘጠኝ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ናይጄሪያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 3 ለ 0 በመርታት ምድቡን እየመራች ነው። በአልጄሪያ የ1 ለ 0 ሽንፈት ያስተናገደችው ቦትስዋና ያለ ምንም ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ናይጄሪያ ካሸነፈች ወደ ሩብ ፍጻሜ የሚያስገባትን ትኬት ትቆርጣለች። ቦትስዋና በምድቡ የመጀመሪያ ድሏን ለማስመዝገብ ትጫወታለች። ሁለቱ ሀገራት እ.አ.አ በ2022 ሞሮኮ ባዘጋጀችው 12ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ ሶስት ተገናኝተው ናይጄሪያ 2 ለ 0 ማሸነፏ የሚታወስ ነው። በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው 13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ ስድስተኛ ቀኑን ይዟል።
ፒኤስጂ ሪያል ማድሪድን በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፏል
Jul 10, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ ሁለተኛ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂ ሪያል ማድሪድን 4 ለ 0 በሆነ የሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል። ትናንት ማምሻውን በሜትላይፍ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፋቢያን ሩዊዝ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ኡስማን ዴምቤሌ እና ጎንዛሎ ራሞስ ቀሪዎቹን ጎሎች ለፈረንሳዩ ቡድን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። የመጀመሪያዎቹ ሁለት ግቦች የተቆጠሩት የሪያል ማድሪድ ተከላካዮች በሰሩት ስህተት ነው። በጨዋታው ፒኤስጂ በጨዋታው በሪያል ማድሪድ ላይ ከፍተኛ ብልጫ የወሰደ ሲሆን ተጨማሪ ግቦችን ማስቆጠር ይችል ነበር። የሪያል ማድሪዱ ግብ ጠባቂ ቲቦ ኮርቶዋ ያዳናቸው ያለቀላቸው ኳሶች ቡድኑ በሰፊ ጎል እንዳይሸነፍ አድርጎታል። ሁለቱ ግቦችን ያስቆጠረው ፋቢያን ሩዊዝ የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተመርጧል። የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው ፒኤስጂ ለፍጻሜ አልፏል። በፍጻሜው ከቼልሲ ጋር ይጫወታል። የፍጻሜው ጨዋታ እሁድ ሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በሜትላይፍ ስታዲየም ይደረጋል። የፓሪሱ ክለብ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ዋንጫውን ለማንሳት ይፋለማል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የክለቦቹ ባስ መንገድ ላይ በገጠመው የትራፊክ መጨናነቅ 10 ደቂቃ ዘግይቶ መጀመሩ አስገራሚ ሆኗል። ለባለንዶር ሽልማት የታጨው ኡስማን ዴምቤሌ በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን ግቦች ወደ 35 ከፍ አድርጓል። ሪያል ማድሪድ ዓመቱን ያለ ዋንጫ አጠናቋል።
አዘጋጅ ሀገር ሞሮኮ የመጀመሪያ ድሏን አስመዝግባለች
Jul 10, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ መርሃ ግብር ሞሮኮ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ትናንት ማምሻውን በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አምበሏ ጊዝላኔ ቼባክ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርታለች። በውድድሩ ሀትሪክ የሰራች የመጀመሪያ ተጫዋች ሆናለች። በውድድሩ ያስቆጠረቻቸውን ግቦች ወደ አራት ከፍ አድርጋለች። ያስሚን ምራቤት ለሞሮኮ ቀሪዋን ጎል በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥራለች። ሜርቬል ናንጉጂ እና ፍላቪን ማዌቴ ለዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ሞሮኮ በጨዋታው በኳስ ቁጥጥር ከፍተኛ ብልጫ የወሰደች ሲሆን የተሻለ የግብ እድልም ፈጥራለች። ውጤቱን ተከትሎ አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ የመጀመሪያ ድሏን አስመዝግባለች። በአራት ነጥብ ደረጃዋን ከሶስተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጋለች። በምድቡ ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻው አራተኛ ደረጃ ያዛለች። በዚሁ ምድብ በተደረገው ሌላኛው ጨዋታ ዛምቢያ ሴኔጋልን 3 ለ 2 አሸንፋለች። ዛምቢያ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሞሮኮ ከሴኔጋል የምድብ አንድ የመጨረሻ ጨዋታዎች ናቸው።
በሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ዛምቢያ ሴኔጋልን አሸነፈች
Jul 9, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ ጨዋታ ዛምቢያ ሴኔጋልን 3 ለ 2 አሸንፋለች። ማምሻውን በኤል ባቺር ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ባርባራ ባንዳ ሁለት ግቦችን ስታስቆጥር ራቼል ኩንዳናንጂ ቀሪዋን ጎል ለዛምቢያ ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ንጉዌናር ንዳዬ በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ምት ሁለቱን ግቦች ለሴኔጋል አስቆጥራለች። ውጤቱን ተከትሎ ዛምቢያ ምድብ አንድን በአራት ነጥብ እየመራች ነው። ሴኔጋል በሶስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። የሴኔጋሏ አጥቂ ንጉዌናር ንዳዬ በውድድሩ ያስቆጠረቻቸውን የግብ ብዛት ወደ አራት ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራች ነው። የዛምቢያዋ የፊት መስመር ተሰላፊ ባርባራ ባንዳ በሶስት ግቦች ትከተላለች። በዚሁ ምድብ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከአዘጋጇ ሞሮኮ ጋር በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሞሮኮ በአንድ ነጥብ ሶስተኛ፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛለች።
የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ዙር ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ
Jul 9, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው 13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ከአንድ ቀን እረፍት በኋላ በምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ይመለሳል። በምድብ አንድ ሴኔጋል ከዛምቢያ ምሽት 1 ሰዓት ላይ በኤል ባቺር ስታዲየም ይጫወታሉ። ሴኔጋል በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት በማሸነፍ ምድቡን በሶስት ነጥብ እየመራች ነው። የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈች ሴኔጋል ለሩብ ፍጻሜ ታልፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ከአዘጋጇ ሞሮኮ ጋር ሁለት አቻ የተለያየችው ዛምቢያ በውድድሩ ለመቆየት ማሸነፍ ግድ ይላታል። ሁለቱ ሀገራት እ.አ.አ ሞሮኮ ባሰናዳችው 12ኛው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ተገናኝተው ነበር። በመደበኛ 90 ደቂቃ አንድ አቻ ተለያይተው ጨዋታው ወደ መለያ ምት አምርቶ ዛምቢያ በመለያ ምት 4 ለ 2 አሸንፋ ለግማሽ ፍጻሜ አልፋለች። በዚሁ ምድብ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከአዘጋጇ ሞሮኮ በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ዴሞክራቲክ ኮንጎ ያለ ምንም ነጥብ ሶስተኛ፣ ሞሮኮ በአንድ ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል። ማሸነፍ ሀገራቱ ወደ ሩብ ፍጻሜ የመግባታቸውን እድል ያሰፋል። ቡድኖቹ ከዚህ ቀደም በሁለት ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታዎች ተገናኝተው ሞሮኮ በሁለቱም አጋጣሚ አሸንፋለች።
“ ከፍጻሜው በፊት የፍጻሜ ጨዋታ” የተባለው የፒኤስጂ እና ሪያል ማድሪድ ፍልሚያ ተጠባቂ ነው
Jul 9, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ ፒኤስጂ እና ሪያል ማድሪድ ዛሬ የሚያደርጉት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪያንን ቀልብ ስቧል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሜትላይፍ ስታዲየም ይካሄዳል። ፒኤስጂ በሩብ ፍጻሜው ባየር ሙኒክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ቡድኑ ሁለት ተጫዋች በቀይ ወጥቶበት ያስመዘገበው ውጤት አድናቆት አስችሮታል። ተጋጣሚው ሪያል ማድሪድ ቦሩሲያ ዶርትሙንድን በሩብ ፍጻሜው 3 ለ 2 በማሸነፍ አራት ውስጥ ገብቷል። ማድሪድ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች የተቆጠሩበት ግቦች ስጋት ውስጥ ከተውት ነበር። የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው ፒኤስጂ በሉዊስ ኤነሪኬ እየተመራ በዘንድሮው የውድድር አስደናቂ ብቃቱን እያሳየ ይገኛል። የፈረንሳይ ሊግ እና የፈረንሳይ ጥሎ ማለፍን ክብር በእጁ ያስገባው የፓሪሱ ክለብ የአውሮፓውን ቁንጮ ውድድር አሸንፏል። ድንቁን ዓመት የዓለም እግር ኳስ ትልቁን ክብር በማሸነፍ የመደምደም ህልም አለው። የ15 ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው ሪያል ማድሪድ ያለ ዋንጫ ያጠነቀቀ ሲሆን አሰልጣኝ ዣቪ አሎንሶ ቡድኑ ከተረከቡት በኋላ ጥሩ መሻሻል አሳይቷል። የአማካይ ክፍል የኳስ ቁጥጥር እና ፈጣን የማጥቃት ሽግግር ከክንፍ መስመር ተጫዋቾች ፈጣን እንቅሰቃሴ ጋር ተጣሮ ሎስ ብላንኮሶቹን ጥንካሬውን መልሶ እንዲያገኝ እያደረጉት ነው። ሁለቱ የአውሮፓ ኃያላን እስከ አሁን በውድድር ጨዋታዎች 13 ተገናኝተው ሪያል ማድሪድ 6 ጊዜ ሲያሸንፍ ፒኤስጂ 3 ጊዜ ድል ቀንቶል ። በሁለት ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይቷል። በዛሬው ጨዋታ በሩብ ፍጻሜው ወሊያን ፓቾ እና ቲኦ ሄርናንዴዝን በቀይ ካርድ ያጣው ፒኤስጂ ተከላካዩ ላይ መጠነኛ መሳሳት ሊያጋጥመው ይችላል። ለባለንዶር የታጨው ኡስማን ኤምቤሌ ወደ ሙሉ የአካል ብቃት እና የጨዋታ ዝግጁነት መመለሱ ለፈረንሳዩ ቡድን መልካም ዜና ነው። ተጋጣሚው ሪያል ማድሪድ በሩብ ፍጻሜ ቀይ ካርድ ያየውን ዲን ሀውሰን አገልግሎት የማያገኝ ሲሆን በሱ ምትክ ራኡል አሴንሲዮ እና ኤደር ሚሊታኦ ሊሰለፉ ይችላሉ የሚሉ ግምቶች እየወጡ ነው። የኪሊያን ምባፔ ወደ መመለስ ለነጮቹ የምስራች የሆነላቸው ሲሆን አጥቂው ከዓመት በፊት በነጻ ዝውውር የለቀቀውን የቀድሞ ቡድኑን ይገጥማል። በአማካይ ክፍሉ ቪቲንሃ፣ ጆአ ኔቬስ እና ፋቢያን ሩዊዝ ከፒኤስጂ፣ ጁድ ቤሊንግሃም፣ ፌዴሪኮ ቫልቬርዶ እና አርዳ ጉለር ከሪያል ማድሪድ የሚኖራቸው ፍጥጫ የበለጠ አጓጊ ሆኗል። እጅግ ጠንካራ እና ተቀራራቢ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ በሚጠበቀው ጨዋታ ፒኤስጂ በጠበበ ሁኔታም ቢሆን ሊያሸንፍ ይችላል የሚሉ ግምቶች እየወጡ ነው። የ44 ዓመቱ ፖላንዳዊ ሲሞን ማርሲኒያክ ተጠባቂውም ፍልሚያ በመሐል ዳኝነት ይመሩታል። የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ በፍጻሜው ከቼልሲ ጋር ይጫወታል።
ቼልሲ ለፍጻሜ አለፈ
Jul 9, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ቼልሲ ፍሉሜኔንሴን 2 ለ 0 አሸንፏል። በሜትላይፍ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በ የ60 ሚሊዮን ፓውንድ ፈራሚው ጆአኦ ፔድሮ በ18ኛው እና 56ኛው ደቂቃ ላይ በግሩም ሁኔታ ያስቆጠራቸው ግቦች ቡድኑን አሸናፊ አድርጓል። ፔድሮ የልጅነት ክለቡ ላይ ግቦቹን ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን በተቀዛቀዘ መልኩ ገልጿል። ጨዋታው ተመጣጣኝ እና ጠንካራ ፉክክር ተደርጎበታል። ቼልሲ ለግብ የቀረቡ እድሎችን በመፍጠር የተሻለ ነበር። ጠንካራው የፍሉሜንሴ የተከላካይ መስመር በጨዋታው ላይ ባልተለመደ ሁኔታ ስህተቶችን ሲሰራ ተስተውሏል። ቡድኑ ከ11 ጨዋታዎች በኋላ ሽንፈት አስተናግዷል። የቼልሲ የአማካይ ተጫዋች ሞሰስ ካሲዬዶ በጉዳት ምክንያት በጨዋታው ማብቂያ ላይ ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። ዋንጫውን ለማንሳት ከፒኤስጂ እና ሪያል ማድሪድ አሸናፊ ጋር ያደርጋል። ፒኤስጂ እና ሪያል ማድሪድ ነገ የሚያደርጉት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
በመዲናዋ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ
Jul 8, 2025 123
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። በዛሬው ዕለት በ11 ክፍለ ከተሞች ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎባቸው የተገነቡ 122 የስፖርት ማዘውተሪያ እና 1ሺህ 155 የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዛሬ ማለዳ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ መሪ ሎቄ 40/60 ኮንዶሚኒየም አካባቢና በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት መጫወቻ መሰረተ ልማቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። ከንቲባዋ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ከተማ አስተዳደሩ በ2017 በጀት ዓመት 15ሺህ 960 ፕሮጀክቶች ገንብቶ አጠናቋል። መሰረተ ልማቶቹን ለመገንባት ከወጣው ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ 50 በመቶ የሚሆነው በከተማዋ ነዋሪዎች መሸፈኑን ነው የተናገሩት። አስተዳደሩ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ3ሺህ 800 በላይ የህፃናት የመጫወቻ ስፍራዎችን መገንባቱንም ገልጸዋል። ጊዜን፣ እውቀትንና የማህበረሰቡን ተሳትፎ በማቀናጀት ለህፃናት እና ለወጣቶች ቅድሚያ በመስጠት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል። ስራዎቹ ህፃናትና ወጣቶች በአካልና በአዕምሮ ብቁ ሆነው እንዲያድጉ የሚያስችሉ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በቀጣይ በስፖርቱ ዘርፍ በዓለምና በአህጉር መድረክ የተሻለ ውጤት ለማምጣት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ በላይ ደጀን በበኩላቸው፤ በከተማዋ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በአዕምሮና በአካል የዳበረ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመገንባት ተቀሜታቸው የጎላ ነው ብለዋል።
ፍሉሜኔንሴ እና ቼልሲ ለክለቦች የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ለማለፍ ይፋለማሉ
Jul 8, 2025 86
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ የግማሽ ፍጻሜ መርሃ ግብር ፍሉሜኔንሴ እና ቼልሲ ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሜትላይፍ ስታዲየም ይካሄዳል። የብራዚሉ ፍሉሜኔንሴ በሩብ ፍጻሜው የሳዕዲ አረቢያውን አል ሂላልን 2 ለ 1 አሸንፏል። የእንግሊዙ ቼልሲ የብራዚሉን ፓልሜራስ 2 ለ 1 በመርታት የመጨረሻ አራት ውስጥ ገብቷል። ባለፉት 11 ጨዋታዎችን ሽንፈትን ያላየው ፍሉሜኔንሴ በዓለም ዋንጫው ግምቶችን ፉርሽ በማድረግ ግማሽ ፍጻሜ ደርሷል። ጠንካራ የተከላካይ ክፍል መስመሩ እና የመልሶ ማጥቃት የአጨዋወት ስልቱ ለተጋጣሚው ራስ ምታት ሆኗል። በሬናቶ ጋውቼ የሚመራው ፍሉሚኔንሴ በባለፈው የውድድር ዓመት በብራዚል ሴሪ አ ከመውረድ ተርፎ በአጭር ጊዜ እያሳየ ያለው አስገራሚ ብቃት አሰልጣኙን አስወድሷቸዋል። የኢንዞ ማሬስካው ቼልሲ በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ በአማካይ ተጫዋቹ የፈጠራ አቅም፣ የታክቲክ ተለዋዋጭነት እና የኳስ የመቆጣጠር አቅም ታግዞ ጥሩ ግስጋሴ እያደረገ ይገኛል። ይሁንና የተከላካይ ክፍል መስመሩ ተጋላጭነት ተጋጣሚዎቹ ግብ እንዲያስቆጥርበት ሲያደርጉ ለመመልከት ተችሏል። ሁለቱ ቡድኖች እርስ በእርስ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የእግር ኳስ ልሂቃኑ እና ተመልካቹ ለቼልሲ የማሸነፍ እድሉን በስፋት ቢሰጡም ተጋጣሚው ፍሉሜኔንሴ ያልተጠበቀ ድል ሊያስመዘግብበት እድል አለ የሚሉ አልጠፉም። ቼልሲ ጨዋታውን ለማሸነፍ ጠንካራውን የብራዚል ክለብ የመከላከል ግድግዳ ማፍረስ ይጠበቅበታል። ፍሉሜኔንሴ ጠንካራ የመከላከል ቅርጹን ጠብቆ በሚያገኛቸው አጋጣሚዎች በመልሶ ማጥቃት ግቦችን ለማስቆጠር የሚያስችል የጨዋታ ስልት ወደ ሜዳ ይዞ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። የፍሉሜንሴው ብራዚላዊ የ40 ዓመት አምበል ቲያጎ ሲልቫ የቀድሞ ክለቡን ቼልሲን የሚገጥምበት ጨዋታ መሆኑንም ትኩረት ስቧል። የ36 ዓመቱ ፈረተንሳዊ ፍራንስዊ ሌቲክሲየር ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ በፍጻሜው ከፒኤስጂ ወይም ከሪያል ማድሪድ አሸናፊ ጋር ይገናኛል። በአሜሪካ አስተጋጅነት እየተካሄደ ያለው የፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ ዛሬ 22ኛ ቀኑን ይዟል።
በሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ማሊ ታንዛንያን አሸነፈች
Jul 8, 2025 90
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት ጨዋታ ማሊ ታንዛንያን 1 ለ 0 አሸንፋለች ። ማምሻውን በቤርካኔ ሙኒሲፓል ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አጥቂዋ ሳራቱ ትራኦሬ በመጀመሪያ አጋማሽ ጭማሪ ደቂቃዎች ላይ የማሸነፊያዋን ጎል አስቆጥራለች። ማሊ በጨዋታው ብልጫ ቢወሰድባትም ያስቆጠረችውን ብቸኛ ግብ አስጠብቃ ወጥታለች። ታንዛንያ በጨዋታው ላይ የነበራትን የተሻለ የኳስ ቁጥጥር እና ኢላማቸውን የጠበቁ ሙከራዎች ወደ ግብ መቀየር አልቻለችም። ውጤቱን ተከትሎ ማሊ በምድብ ሶስት በሶስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። በዚሁ ምድብ ዛሬ በተካሄደው የመጀመሪያ ጨዋታ የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት ደቡብ አፍሪካ ጋናን 2 ለ 0 አሸንፋለች። የምድቡ መሪም ሆናለች። ጋና ከማሊ፣ ታንዛንያ ከደቡብ አፍሪካ በምድቡ የሚደረጉ ቀጣይ ጨዋታዎች ናቸው።
ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካ ዋንጫ ክብር የማስጠበቅ ጉዞዋን በድል ጀምራለች
Jul 7, 2025 112
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት የመጀመሪያ መርሃ ግብር ደቡብ አፍሪካ ጋናን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በሆነር ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሊንዳ ሞትልሃሎ በፍጹም ቅጣት ምት እና ጀርሜን ሲኦፖሴንዌ በጨዋታ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር የተደረገበት ሲሆን ደቡብ አፍሪካ ያገኘችውን የግብ እድል በሚገባ መጠቀሟ ባለድል አድርጓታል። ውጤቱን ተከትሎ የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ደቡብ አፍሪካ ጉዞዋን በድል ጀምራለች። ምድቧንም በሶስት ነጥብ እየመራች ነው። ጋና ያለ ምንም ነጥብ በምድቡ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች።