ስፖርት - ኢዜአ አማርኛ
ስፖርት
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መሪው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ነጥብ ጣለ
Feb 22, 2026 56
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የሁለተኛ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ተደርገዋል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና መቻል ያደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ነጥቡን ወደ 37 ከፍ አድርጓል። ከተከታዩ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለውን የነጥብ ልዩነት የማስፋት እድል አልተጠቀመበትም። መቻል በ30 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። በሌላ መርሐ-ግብር ድሬዳዋ ከተማ ባህርዳር ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል። ኤልሳ መኮንን በ56ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥራለች። ድሬዳዋ ከተማ በ16 ነጥብ ደረጃውን ከ9ኛ ወደ 8ኛ ከፍ አድርጓል። ባህር ዳር ከተማ በ10 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር አቻ ተለያየ
Feb 22, 2026 53
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ጨዋታው ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ተካሂዷል። ውጤቱን ተከትሎ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ነጥቡን ወደ 36 ከፍ አድርጓል። ቡድኑ ባለፉት አራት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ18 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ሃዋሳ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ሽመልስ በቀለ ለሃዋሳ ከተማ፣ ድልአዲስ ገብሬ ለድሬዳዋ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሃዋሳ ከተማ በ36 ነጥብ ሁለተኛ፣ ድሬዳዋ ከተማ በ25 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዘዋል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው ጨዋታ ሸገር ከተማ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ሸገር ከተማ በ22 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ28 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። አርባምንጭ ከተማ እና ነገሌ አርሲ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቋል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተደረገው ጨዋታ በፍቅር ግዛቸው ለአርባምንጭ ከተማ፣ ዳዊት ተፈራ ለነገሌ አርሲ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። አርባምንጭ ከተማ በ13 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። አዲስ አዳጊው ነገሌ አርሲ በ36 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
በሰሜን ለንደን ደርቢ አርሰናል ቶተንሃም ሆትስፐርስን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ
Feb 22, 2026 97
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐ-ግብር አርሰናል ቶተንሃም ሆትስፐርስን 4 ለ 1 ረትቷል። በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መሪው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ነጥብ ጣለ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር አቻ ተለያየ ማምሻውን በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኤበረቺ ኢዜ እና ቪክቶር ዩኮሬሽ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል። ራንዳል ኮሎ ሙዋኒ ለስፐርስ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው አርሰናል በተጋጣሚው ላይ ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል። ቶተንሃም ሆትስፐርስ በሁለተኛው አጋማሽ ግብ ለማስቆጠር ያደረጋቸው ጥረቶች አልተሳኩም። ከሁለት ተከታታይ የአቻ ውጤቶች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው አርሰናል ነጥቡን ወደ 61 ከፍ በማድረግ መሪነቱን አጠናክሯል። በሊጉ 18ኛ ድሉን አስመዝግቧል። ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 12ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ29 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። የፈረንጆች 2026 ከገባ በኋላ ምንም ድል ያላስመዘገበው ስፐርስ ባለፉት ዘጠኝ የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። በጨዋታው ላይ ሁለት ግቦችን ያስቆጠረው ኤበረቺ ኢዜ ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ሀትሪክ መስራቱ የሚታወስ ነው። ዛሬ በተደረጉ በሌሎች ጨዋታዎች ሊቨርፑል ኖቲንግሃም ፎረስትን፣ ክሪስታል ፓላስ ዎልቭስን በተመሳሳይ 1 ለ 0 አሸንፈዋል። ፉልሃም ሰንደርላንድን 3 ለ 1 ረቷል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ነገ ኤቨርተን እና ማንችስተር ዩናይትድ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል።
ተጠባቂው የቶተንሃም ሆትስፐርስ እና አርሰናል የሰሜን ለንደን ደርቢ ፍልሚያ
Feb 22, 2026 90
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/ 2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐ-ግብር ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከአርሰናል ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ጨዋታው ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየም ይካሄዳል። ቶተንሃም ሆትስፐርስ በሊጉ 26 ጨዋታዎች አድርጎ በሰባቱ ሲያሸንፍ በ11ዱ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ ስምንት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 36 ግቦችን በ26ቱ ጨዋታዎች ላይ ሲያስቆጥር 37 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ስፐርስ በ29 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። አርሰናል በሊጉ እስከ አሁን ካከናወናቸው 27 ጨዋታዎች 17 ቱን ሲያሸንፍ ሶስት ጊዜ ተሸንፏል። ሰባት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥቷል። 52 ግቦችን ሲያስቆጥር 20 ጎሎችን አስተናግዷል። አርሰናል በ58 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዟል። የሰሜን ለንደኖቹ አርሰናል እና ቶተንሃም ሆትፐርስ 129 ዓመታትን ያስቆጠረ የተቀናቃኝነት ታሪክ አላቸው። ቡድኖቹ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኙነት እ.አ.አ በ1896 ሲሆን በወቅቱ ዩናይትድ ሊግ በሚባለው የውድድር ፎርማት ላይ ተጫውተው አርሰናል (በወቅቱ አጠራሩ ዎልዊች አርሰናል) ቶተንሃም ሆትስፐርስን 2 ለ 1 አሸንፏል። እ.አ.አ በ1897 በዩናይትድ ሊግ ተገናኝተው ቶተንሃም ሆትስፐርስ 3 ለ 2 በማሸነፍ በአርሰናል ላይ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል። ቡድኖቹ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ባስቆጠረው ተቀናቃኝነታቸው እስከ አሁን በሁሉም ውድድሮች 212 ጊዜ ተገናኝተዋል። በዚህም አርሰናል 90 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ቶተንሃም ሆትስፐርስ 67 ጊዜ አሸንፎ 55 ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። በፕሪሚየር ሊጉ 67 ጊዜ ባደረጓቸው የእርስ በእርስ ጨዋታዎች አርሰናል 28 ጊዜ ሲያሸንፍ ቶተንሃም ሆትስፐርስ 15 ጊዜ ድል ቀንቶት 24 ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርተዋል። ባለፉት አምስት የሊግ ግንኙነታቸው አርሰናል አራት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። አርሰናል ካሸነፈ ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ከፍ ያደርጋል። ባለፉት ስምንት የሊግ ጨዋታዎች ያላሸነፈው ቶተንሃም ሆትስፐርስ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይፋለማል። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያ ዙር በኤምሬትስ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ አርሰናል 4 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የ43 ዓመቱ ፒተር ባንክስ ተጠባቂውን የደርቢ ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌሎች መርሐ-ግብሮች ኖቲንግሃም ፎረስት ከሊቨርፑል፣ ክሪስታል ፓላስ ከዎልቭስ እና ሰንደርላንድ ከፉልሃም በተመሳሳይ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መሪው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከመቻል የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Feb 22, 2026 71
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከመቻል በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው 13 ጨዋታዎች መካከል 12ቱን ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በ13ቱ ጨዋታዎች 32 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ሰባት ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ36 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። ተጋጣሚው መቻል በበኩሉ 13 ጨዋታዎችን አከናውኖ በዘጠኙ ድል ሲቀናው ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 23 ጎሎችን ሲያስቆጥር ሰባት ግቦች ተጠቆጥረውበታል። መቻል በ29 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና መቻል በዘንድሮው የውድድር ዓመት ጥሩ እንቅስቃሴ እያደረጉ የሚገኙ ክለቦች ናቸው። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ 3 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። በሌላኛው መርሐ-ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከባህር ዳር ከተማ ከቀኑ ሰባት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው 13 ጨዋታዎች መካከል አራቱን ያሸነፈው ድሬዳዋ ከተማ በስምንቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪው አንድ ጨዋታ ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 12 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 21 ግቦችን አስተናግዷል። ድሬዳዋ ከተማ በ13 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ባህር ዳር ከተማ በበኩሉ 14 ጨዋታዎችን አድርጎ በሶስቱ አሸንፎ በዘጠኙ ተሸንፎ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። ስምንት ግቦችን ሲያስቆጥር 16 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ባህር ዳር ከተማ በ10 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያ ዙር በነበራቸው ግንኙነት ባህር ዳር ከተማ 2 ለ 0 ማሸነፉ አይዘነጋም።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር ይጫወታል
Feb 22, 2026 70
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት ሁለተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከመርሐ-ግብሮቹ መካከል ሲዳማ ቡና ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ምሽት 12 ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠቃሽ ነው። ሲዳማ ቡና በ35 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ17 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሲዳማ ቡና ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ድል አልቀናቸውም። ጨዋታው ሁለቱ ቡድኖች ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። ቡድኖቹ በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ሲዳማ ቡና 4 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። በሌላኛው መርሃ ግብር ሃዋሳ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሃዋሳ ከተማ በ35 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ድሬዳዋ ከተማ በ24 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። ሃዋሳ ከተማ በሊጉ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ድሬዳዋ ከተማ ካሸነፈ ወደ አሸናፊነት መንገድ ይመለሳል። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያው ዙር በመጀመሪያ ሳምንት ባደረጉት ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ 2 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። አርባምንጭ ከተማ ከነገሌ አርሲ ከቀኑ 9 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። በሊጉ አንድ ጨዋታ ብቻ ያሸነፈው አርባምንጭ ከተማ በ12 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። ነገሌ አርሲ በ35 ነጥብ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። አርባምንጭ ከተማ በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ነገሌ አርሲ ካሸነፈ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘግባል። ቡድኖቹ በመጀመሪያው ዙር በነበራቸው ግንኙነት አንድ አቻ ተለያይተዋል። ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በ21 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ27 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። ሸገር ከተማ ከ19ኛ ሳምንት የአቻ ውጤት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ባለፉት አራት የሊጉ ጨዋታዎች ያላሸነፈው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሶስት ነጥብ ለማግኘት ይፋለማል። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ 1 ለ 0 ማሸነፉ አይዘነጋም ።
ማንችስተር ሲቲ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል
Feb 21, 2026 89
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በኢትሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የ20 ዓመቱ ታዳጊ ኒኮ ኦራይሊ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥሯል። ሉዊስ ሆል ለኒውካስትል ዩናይትድ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው ማንችስተር ሲቲ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ቢወስድም ሁለቱም ቡድኖች ተቀራራቢ በሚባል ሁኔታ ግልጽ የግብ እድሎችን ፈጥረዋል። ሁለተኛው አጋማሽ ጠንካራ ፉክክር ተደርጎበታል። ውጤቱን ተከትሎ በሊጉ 17ኛ ድሉን ያስመዘገበው ማንችስተር ሲቲ በ56 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ አድርጓል። በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 11ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኒውካስትል ዩናይትድ በ36 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። የሊጉ መሪ አርሰናል ከቶተንሃም ሆትስፐርስ ጋር ነገ ከሜዳው ውጪ የሚያደርገው የሰሜን ለንደን ደርቢ ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አዳማ ከተማ አሸንፈዋል
Feb 21, 2026 73
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ20ኛ ሳምንት ሁለት ጨዋታዎች ማምሻውን ተደርገዋል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን 3 ለ 1 አሸንፏል። ዩጋንዳዊው ሳይመን ፒተር፣ ሁዘይፋ ሻፊ እና ሳምሶን ቹቹ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ታምራት እያሱ ለፋሲል ከነማ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ24 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ፋሲል ከነማ በ33 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሌላኛው መርሐ-ግብር አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አምበሉ ቢንያም አይተን በ61ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ አዳማ ከተማ በ31 ነጥብ አምስተኛ፣ የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ20 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዘዋል። ቀን ላይ በተደረጉ የ20ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3፣ ባህርዳር ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፈዋል።
ቼልሲ እና በርንሌይ ነጥብ ተጋሩ
Feb 21, 2026 73
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ቼልሲ እና በርንሌይ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ማምሻውን በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጆአኦ ፔድሮ በ4ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ግብ ቼልሲን መሪ አድርጓል። ዚያን ፍሌሚንግ በ93ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል ለበርንሌይ አንድ ነጥብ አስገኝታለች። የቼልሲው ዌስሊ ፎፋና በ72ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ሜዳ ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ በ45 ነጥብ ደረጃውን ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። በርንሌይ በ19 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በሌሎች ጨዋታዎች በርንሌይ ብሬንትፎርድን 2 ለ 0 ሲረታ አስቶንቪላ እና ሊድስ ዩናይትድ አንድ አቻ ተለያይተዋል።
ወላይታ ድቻ እና ባህርዳር ከተማ በሊጉ ወደ አሸናፊነት የተመለሱበትን ድል አስመዘገቡ
Feb 21, 2026 75
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር መርሐ-ግብር ዛሬ በ20ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ተጀምሯል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ዛሬ ይጀመራል በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና እና አዲስ አበባ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወላይታ ድቻ ከ2 ለ 0 መመራት ተነስቶ መቻልን 4 ለ 3 አሸንፏል። ዮናታን ኤልያስ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ቴዎድሮስ ኃይለማርያም እና ካርሎስ ዳምጠው ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ለመቻል ቸርነት ጉግሳ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ በረከት ደስታ ቀሪዋን ጎል አስቆጥሯል። ከዘጠኝ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ወላይታ ድቻ በ19 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በውድድር ዓመቱ ሶስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በሊጉ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቻል በ30 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። በሌላ መርሐ-ግብር ባህርዳር ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ግርማ ዲሳሳ በ36ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ከአምስት ተከታታይ የአቻ ውጤቶች በኋላ ወደ ድል መንገድ የተመለሰው ባህርዳር ከተማ ደረጃውን ከዘጠነኛ ወደ ሰባተኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ አምስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በውድድር ዓመቱ ስምንተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሀዲያ ሆሳዕና በ24 ነጥብ ከነበረበት 10ኛ ደረጃ ወደ 11ኛ ዝቅ ብሏል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና እና አዲስ አበባ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል
Feb 21, 2026 82
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14 /2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር መርሐ-ግብር ዛሬ በ14ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ተጀምሯል። የኢትዮጵያ የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኟው ዙር ጅማሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ዛሬ ይጀመራል በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሲዳማ ቡና በዳሳሽ ሰውአገኝ ጎል ቦሌ ክፍለ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል። በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ድሉን ያስመዘገበው ሲዳማ ቡና በ18 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። በአንጻሩ በሊጉ ሶስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ቦሌ ክፍለ ከተማ በ23 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በሌላኛው መርሐ-ግብር አዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አማሩ አብተው እና አለሚ በዬቻ የማሸነፊያ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ሄለን እሸቱ ለልደታ ክፍለ ከተማ ብቸኛውን ግብ አስቆጥራለች። በሊጉ ሁለተኛ ድሉን ያስመዘገበው አዲስ አበባ ከተማ በስምንት ነጥብ የመጨረሻውን 14ኛ ደረጃ ይዟል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ልደታ ክፍለ ከተማ በበኩሉ በተመሳሳይ ስምንት ነጥብ በግብ ክፍያ በልጦ 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ይርጋጨፌ ቡና እና አርባምንጭ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ መታሰቢያ ክፍሌ ለይርጋጨፌ ቡና ፣ ስንዱ ዳምጠው ለአርባምንጭ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ይርጋጨፌ ቡና በ11 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። አርባምንጭ ከተማ በዘጠኝ ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ዛሬ ይጀመራል
Feb 21, 2026 131
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከሁለት ሳምንታት ቆይታ በኋላ ዛሬ በ20ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ይመለሳል። በዕለቱ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በዚህም መሠረት ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፋሲል ከነማ ምሽት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ21 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ፋሲል ከነማ በ33 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሁለቱም ቡድኖች በተመሳሳይ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻሉም። ቡድኖቹ በመጀመሪያው ዙር በመጀመሪያ ሳምንት ባደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ መድን ከአዳማ ከተማ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ20 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። አዳማ ከተማ በ28 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። መድን ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ተጋጣሚው አዳማ ከተማ ባለፉት ሶስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። በሌላኛው መርሐ-ግብር ወላይታ ድቻ ከመቻል ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ወላይታ ድቻ በ16 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። መቻል በ30 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ባለፉት ዘጠኝ ጨዋታዎች ከድል የራቀው ወላይታ ድቻ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ተጋጣሚው መቻል ማሸነፍ ከሁለት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል እንዲመለስ ያደርገዋል። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ መቻል 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ሀዲያ ሆሳዕና ከባህርዳር ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሀዲያ ሆሳዕና በ24 ነጥብ 10ኛ፣ ባህርዳር ከተማ በተመሳሳይ 24 ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ 9ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ባለፉት አራት ጨዋታዎች ያላሸነፈው ሀዲያ ሆሳዕና እና ባለፉት አምስት ጨዋታዎች አቻ የወጣው ባህርዳር ከተማ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ባህርዳር ከተማ 3 ለ 1 ማሸነፉ አይዘነጋም። የ20ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር እስከ የካቲት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና በ20ኛ ሳምንት ሊያደርጉት የነበረው ጨዋታ ወደ ሌላ እንዲሸጋገር መደረጉን የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል። ሲዳማ ቡና በ35 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ አዲስ ግደይ እና የቅዱስ ጊዮርጊሱ አቤል ያለው በተመሳሳይ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመሩ ነው።
ማንችስተር ሲቲ ከኒውካስትል ዩናይትድ ጋር ይጫወታል
Feb 21, 2026 161
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል። በዕለቱ አምስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ዛሬ ይጀመራል ምሽት አምስት ሰዓት ላይ ማንችስተር ሲቲ ከኒውካስትል ጋር በኢትሃድ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ማንችስተር ሲቲ በ53 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ኒውካስትል ዩናይትድ በ36 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ውሃ ሰማያዊዎቹ ሶስተኛ ተከታታይ ድላቸውን ለማስመዘገብ ይጫወታሉ። በ26ኛ ሳምንት ከሜዳው ውጪ ቶተንሃም ሆትስፐርስን 2 ለ 1 ያሸነፈው ኒውካስትል ዩናይትድ ተከታታይ ድል ለማስመዝገብ ይፋለማል። ማንችስተር ሲቲ ካሸነፈ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት በጊዜያዊነት ወደ ሁለት ዝቅ ያደርጋል። በሌላኛው መርሐ-ግብር አስቶንቪላ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሊድስ ዩናይትድን በቪላ ፓርክ ስታዲየም ያስተናግዳል። አስቶንቪላ በ50 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ሊድስ ዩናይትድ በ30 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ጨዋታው አስቶንቪላ በዋንጫ ፉክክሩ ለመቆየት፣ ሊድስ ዩናይትድ ከወራጅ ቀጠና ለመራቅ ሶስት ነጥብ ለማግኘት የሚፋለሙበት ነው። ቼልሲ ከበርንሌይ እና ብሬንትፎርድ ከብራይተን በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። ዌስትሃም ዩናይትድ ከቦርንማውዝ ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ በለንደን ስታዲየም ይጫወታሉ።
ቅድሚያ ለሴቶች የሩጫ ውድድር በመጋቢት ወር ይካሄዳል
Feb 20, 2026 84
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2018 (ኢዜአ)፡- 23ኛው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ቅድሚያ ለሴቶች የአምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ይደረጋል። ይህ በየዓመቱ ለሴቶች ብቻ የሚዘጋጀው የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር መነሻ እና መድረሻው ቦሌ አትላስ ሆቴል መሆኑ ተገልጿል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን አስመልክቶ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ በውድድሩ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። 23ኛው ዓመት ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎ ሜትር ውድድር ነገ ምዝገባ እንደሚጀመር ገልጸው፤ ለሶስት ሳምንታት እንደሚቆይ አመላክተዋል። በውድድሩ ላይ 16 ሺህ ሴቶች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። የሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር፤ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ፣ በኢትዮጵያ የአየርላንድ ኤምባሲ እና በሌሎች የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት ትብብር የተዘጋጀ ነው። ውድድሩ የተጀመረው በ1996 ዓ.ም ነው።
አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ በዓለም የቤት ውስጥ ውድድር በ3000 ሜትር የዓመቱን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸፈች
Feb 20, 2026 136
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2018(ኢዜአ)፦ በፈረንሳይ ላይቪን የቤት ውስጥ የአትሌቲክስ ውድድር ተካሄዷል። በሴቶች 3000 ሜትር አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ በ8 ደቂቃ ከ24 ሴኮንድ ከ59 ማይክሮ ሴኮንድ አሸንፋለች። በርቀቱም የ2026 ፈጣን ሰዓት አስመዝግባለች። አለሺኝ ባወቀ ሁለተኛ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ስትጨርስ ጣልያናዊቷ ናዲያ ባቶክሌቲ ሶስተኛ ወጥታለች። በውድድሩ ሂሩት ማስረሻ አምስተኛ፣ ሃዊ አበራ ስድስተኛ፣ የኔዋ ንብረት ዘጠነኛ፣ ብርቱካን ሞላ 10ኛ፣ ሺቶ ጉሚ 11ኛ፣ ፋንታዬ በላይነህ 13ኛ እና አስቴር አረሪ 14ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በወንዶች የ3000 ሜትር ውድድር አትሌት አዲሱ ይሁኔ 7 ደቂቃ ከ33 ሴኮንድ ከ58 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት አንደኛ ወጥቷል። ኬንያዊው ጃኮብ ኪሮፕ ሁለተኛ እና ጌትነት ዋለ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በ1500 ሜትር ሴቶች ብርቄ ኃየሎም እና ሳሮን በርሄ ሁለተኛና ሶስተኛ ወጥተዋል። የታላቋ ብሪታኒያ አትሌት ጆርጂያ ሃንተር ቤል ውድድሩን አሸንፋለች። ወርቅነሽ መሰለ እና ሐረገወይን ካላዩ 9ኛ እና 10ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል። በሴቶች 2000 ሜትር ኬና ቱፋ አምስተኛ፣ ባይሴ ቶሎሳ 10ኛ እና ገላ ሐምበሴ 11ኛ ወጥተዋል። አውስትራሊያዊቷ ጄሲካ ሁል፣ ፖርቹጋላዊቷ ሳሎሜ አልፎንሶ እና ፈረንሳያዊቷ አጋት ጉሌሞት ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል። በሴቶች 800 ሜትር አትሌት ፅጌ ዱጉሞ ሶስተኛ ወጥታለች። ንግስት ጌታቸው አራተኛ ደረጃን ይዛለች። የታላቋ ብሪታኒያ አትሌት ኬሊ ሆድኪንሰን አንደኛ ስትወጣ ስዊዘርላንዳዊቷ ኦውድሬይ ዌሮ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። የዓለም አትሌቲክስ እ.አ.አ በ2026 ባወጣው መርሐ-ግብር አማካኝነት በተለያዩ ሀገራተ የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድሮች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ።
በሻምፒዮንስ ሊጉ ቦዶ ግሊምት እና ባየር ሌቨርኩሰን ድል ቀናቸው
Feb 19, 2026 107
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11 /2018(ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ መርሐ-ግብር ማምሻውን ሶስት ጨዋታዎች ተከናውነዋል። በአስፕማይራ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቦዶ ግሊምት ኢንተር ሚላንን ባልተጠበቀ ሁኔታ 3 ለ 1 አሸንፏል። ሶንድሬ ብሩንስታድ ፌት፣ ጄንስ ፒተር ሃውግ እና ካስፐር ዋርትስ ሆግ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ፍራንቼስኮ ፒዮ ኤስፖዚቶ ለኢንተር ሚላን ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ባየር ሌቨርኩሰን ከሜዳው ውጭ በፓትሪክ ሺክ ግቦች ኦሎምፒያኮስን 2 ለ 0 ረቷል። ክለብ ብሩዥ እና አትሌቲኮ ማድሪድ ሶስት አቻ ተለያይተዋል። በጃን ብሬይዴል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ክሪስቶስ ዞሊስ፣ ኒኮሎ ትሪሶልዲ እና ራፋኤል ኦንዬዲካ ለብሩዥ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጁሊያን አልቫሬዝ፣ አዴሞላ ሉክማን እና የክለብ ብሩዡ ጆኤል ኦርዶኔዝ በራሱ ላይ ለአትሌቲኮ ማድሪድ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ክለብ ብሩዥ ሁለት ጊዜ ተመርቶ አቻ ወጥቷል። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ኒውካስትል ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ካራባግን 6 ለ 1 ረቷል። የመልስ ጨዋታዎች በቀጣይ ሳምንት ይካሄዳሉ።
የሊጉ መሪ አርሰናል ከዎልቭስ ጋር አቻ ተለያየ
Feb 19, 2026 110
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ31ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ዎልቭስ እና አርሰናል ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ማምሻውን በሞልኒው ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቡካዮ ሳካ እና ፒዬሮ ሂንካፒዬ ለአርሰናል ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሁጎ ቡዌኖ እና የአርሰናሉ ተከላካይ ሪካርዶ ካላፊዮሪ በራሱ ላይ ለዎልቭስ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ከ2 ለ 0 መምራት አቻ የወጣው አርሰናል በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ነጥብ ጥሏል። በጨዋታው አርሰናል የተሻለ ብልጫ ነበረው። የሊጉ መሪ አርሰናል ነጥቡን ወደ 58 ነጥብ ከፍ አድርጓል። ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት በጊዜያዊነት ወደ አምስት ከፍ አድርጓል። ዎልቭስ በ10 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ዎልቭስ በውድድር ዓመቱ ያሸነፈው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። የሁለቱ ቡድኖች የ31ኛ ሳምንት ጨዋታ ዛር የተደረገው አርሰናል ከማንችስተር ሲቲ ጋር ያለበት የካራባኦ ዋንጫ ከመርሐ-ግብሩ ጋር በመገጣጠሙ ምክንያት ማስተካከያ ተደርጎበት ነው።
በሻምፒዮንስ ሊጉ ኒውካስትል ዩናይትድ ካራባግን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ
Feb 18, 2026 94
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2018(ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ መርሐ-ግብር ኒውካስትል ዩናይትድ ካራባግን 6 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በቶፊቅ ባህራሞቭ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አንቶኒ ጎርደን ሁለት በጨዋታ እና ሁለት በፍጹም ምት በአጠቃላይ አራት ጎሎችን አስቆጥሯል። ማሊክ ታው እና ጃኮብ መርፊ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኤልቪን ጃፋርኩሊዬቭ ለካራባግ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ኒውካስትል ዩናይትድ በጨዋታው ላይ ከፍተኛ ብልጫ ወስዷል። አራት ግቦችን ያስቆጠረው አንቶኒ ጎርደን የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተመርጧል። ውጤቱን ተከትሎ ኒውካስትል ዩናይትድ ጥሎ ማለፉ የመቀላቀል እድሉን የበለጠ አስፍቷል። የሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታ በቀጣዩ ሳምንት ይካሄዳል።
በሻምፒዮንስ ሊጉ ኒውካስትል ዩናይትድ ካራባግን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ
Feb 18, 2026 85
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11 /2018(ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ መርሐ-ግብር ኒውካስትል ዩናይትድ ካራባግን 6 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በቶፊቅ ባህራሞቭ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አንቶኒ ጎርደን ሁለት በጨዋታ እና ሁለት በፍጹም ምት በአጠቃላይ አራት ጎሎችን አስቆጥሯል። ማሊክ ታው እና ጃኮብ መርፊ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኤልቪን ጃፋርኩሊዬቭ ለካራባግ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ኒውካስትል ዩናይትድ በጨዋታው ላይ ከፍተኛ ብልጫ ወስዷል። አራት ግቦችን ያስቆጠረው አንቶኒ ጎርደን የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተመርጧል። ውጤቱን ተከትሎ ኒውካስትል ዩናይትድ ጥሎ ማለፉ የመቀላቀል እድሉን የበለጠ አስፍቷል። የሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታ በቀጣዩ ሳምንት ይካሄዳል።
የሊጉ መሪ አርሰናል ከዎልቭስ ጋር ይጫወታል
Feb 18, 2026 145
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2018 (ኢዜአ)፡- ዎልቨርሃምፕተን ዎንድረርስ ከአርሰናል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ31ኛ ሳምንት ጨዋታቸውን ዛሬ ያደርጋሉ። ጨዋታው ምሽት አምስት ሰዓት ላይ በሞልኒው ስታዲየም ይካሄዳል። ዎልቭስ በዘጠኝ ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። አርሰናል በ57 ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው 26 ጨዋታዎች መካከል አንዱን ብቻ ያሸነፈው ዎልቭስ 19 ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በስድስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 16 ግቦችን ሲያስቆጥር 48 ጎሎችን አስተናግዷል። ተጋጣሚው አርሰናል በበኩሉ 26 ጨዋታዎችን አድርጎ በ17ቱ ድል ሲቀናው ሶስት ጊዜ ተሸንፏል። ስድስት ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። 50 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያገናኝ 18 ጎሎች ገብተውበታል። ዎልቭስ በሊጉ ሁለተኛ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። መርሐ-ግብሩ አርሰናል በ26ኛ ሳምንት ከብሬንትፎርድ ጋር አቻ ከወጣበት ጨዋታ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ የሚያደርገው ነው። መድፈኞቹ ካሸነፉ ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያላቸውን የነጥብ ልዩነት በጊዜያዊነት ወደ ሰባት ከፍ ያደርጋሉ። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያው ዙር በኤምሬትስ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ አርሰናል 2 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ሁለቱ ቡድኖች የ31ኛ ሳምንት ጨዋታቸውን ሊያደርጉ የነበረው በመጋቢት ወር 2018 ዓ.ም ነበር። ይሁንና አርሰናል በካራባኦ ፍጻሜ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ጨዋታ የሚያደርግበት ወቅት ከ31ኛው ሳምንት መርሐ-ግብር ጋር በመጋጨቱ ምክንያት ጨዋታው ላይ ማስተካካያ ተደርጎበታል።