ቀጥታ፡
ስፖርት
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከምድረ ገነት ሽሬ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል  
Mar 13, 2026 35
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል። በዕለቱ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡና ከምድረ ገነት ሽሬ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ ካከናወናቸው 23 ጨዋታዎች መካከል 11ዱን ሲያሸንፍ ሶስት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ ዘጠኝ ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 28 ግቦችን ሲያስቆጥር 14 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ42 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። በሊጉ ካደረጋቸው 24 ጨዋታዎች መካከል ስምንቱን ያሸነፈው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በበኩሉ አምስት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በ10 ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 17 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 13 ግቦች ተቆጥረውበታል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ34 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሲዳማ ቡና በ23ኛ ሳምንት በወላይታ ድቻ ካስተናገደው የ3 ለ 1 ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ድል ከቀናው ከተከታዩ ሃዋሳ ከተማ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ነጥብ ከፍ ያደርጋል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካሸነፈ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘግባል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ፋሲል ከነማ ከመቻል ከቀኑ 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ፋሲል ከነማ በሊጉ 23 ጨዋታዎችን በማድረግ ስምንት ጊዜ ሲያሸንፍ በአምስቱ ተሸንፏል። 10 ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 17 ግቦችን ሲያስቆጥር 15 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ34 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። መቻል በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው 23 ጨዋታዎች በዘጠኙ ድል ሲቀናው ስድስት ጊዜ ተሸንፏል። በስምንት ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። 29 ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ 19 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ35 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። መቻል በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርካታ ግቦችን ያስቆጠረ ክለብ ነው። ፋሲል ከነማ ባለፉት ስድስት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። መቻል በ23ኛ ሳምንት ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ሁለቱ ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ጨዋታ ተመጣጣኝ ፉክክር ይደርግበታል ተብሎ ይጠበቃል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከባህርዳር ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ25 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት ሰባት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ባህር ዳር ከተማ በ28 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ ይጫወታሉ። ሀዲያ ሆሳዕና ከሸገር ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሀዲያ ሆሳዕና በ29 ነጥብ ዘጠነኛ፣ ሸገር ከተማ በ27 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዘዋል። ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አቻ የወጣው ሀዲያ ሆሳዕና ወደ ድል ለመመለስ ይጫወታል። ሸገር ከተማ ካሸነፈ ተከታታይ ድሉን ያስመዘግባል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት እስከ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን የሲዳማ ቡናው አቤል ያለው እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ አዲስ ግደይ በተመሳሳይ ዘጠኝ ግቦችን በማስቆጠር በጋራ እየመሩ ነው። የፋሲል ከነማው ታምራት ኢያሱ በስምንት ግቦች ይከተላል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሃዋሳ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ መቻል ከአርባምንጭ ከተማ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ተጠባቂ ናቸው
Mar 12, 2026 76
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል። ሃዋሳ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ።   በሊጉ እስከ ካደረጋቸው 17 ጨዋታዎች መካከል 10ሩን ያሸነፈው ሃዋሳ ከተማ በሁለቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች ላይ አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 31 ግቦችን ሲያስቆጥር 12 ጎሎችን አስተናግዷል። ሃዋሳ ከተማ በ35 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ድሬዳዋ ከተማ በውድድር ዓመቱ 17 ጨዋታዎችን አከናውኖ በስድስቱ ድል ሲቀናው 10 ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ አንድ ጨዋታ ነጥብ ተጋርቷል። 16 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 27 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ድሬዳዋ ከተማ በ19 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በ17ኛ ሳምንት ሃዋሳ ከተማ አዲስ አበባ ከተማን 3 ለ 1 አሸንፏል። ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክክትሪክ የ3 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል። ጨዋታው ሃዋሳ ከተማ በድል ጉዞው ለመቀጠል ድሬዳዋ ከተማ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። በሌላኛው መርሐ-ግብር መቻል ከአርባምንጭ ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።   መቻል እስከ አሁን በሊጉ 17 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን 10 ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። በአምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በ17ቱ ጨዋታዎች ላይ 27 ጎሎችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 10 ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ35 ነጥብ አምስተኛ ይዟል። ተጋጣሚው አርባምንጭ ከተማ በበኩሉ ካከናወናቸው 17 ጨዋታዎች መካከል ሁለት ጊዜ ድል ሲቀናው በ11ዱ ተሸንፏል። በቀሪ አራት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 10 ግቦችን ሲያስቆጥር 29 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አርባምንጭ ከተማ በ10 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። መቻል በ17ኛ ሳምንት ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል። አርባምንጭ ከተማ ከአዳማ ከተማ ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ጨዋታው መቻል ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ አርባምንጭ ከተማ ወደ ድል መንገድ ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። ሲዳማ ቡና ከባህርዳር ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ።   ሲዳማ ቡና በ21 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ባህርዳር ከተማ በ10 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ክለቦች በ17ኛ ሳምንት ካጋጠማቸው ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይፋለማሉ።
በተጠባቂው ጨዋታ ሪያል ማድሪድ ማንችስተር ሲቲን አሸነፈ
Mar 12, 2026 123
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ መርሐ-ግብር ሪያል ማድሪድ ማንችስተር ሲቲን 3 ለ 0 ረቷል። በበርናባው ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፌዴሪኮ ቫልቫርዴ በ20ኛው፣ በ27ኛው እና በ42ኛው ደቂቃ ግቦቹን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። ባየር ሌቨርኩሰን እና አርሰናል አቻ ተለያዩ ሪያል ማድሪድ በ58ኛው ደቂቃ ያገኘውን ፍጹም ቅጣት ምት ቪኒሺየስ ጁኒየር መጠቀም ሳይችል ቀርቷል። በጨዋታው ሪያል ማድሪድ በተጋጣሚው ላይ ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል። ግልጽ የግብ እድሎችን መፍጠር ያልቻለው እና የተከላካይ ክፍሉ ስህተት ሲሰራ የነበረው ማንችስተር ሲቲ ደካማ እንቅስቃሴ አድርጓል። ኪሊያን ምባፔ እና ጁድ ቤሊንግሃምን ጨምሮ ቁልፍ ተጫዋቾቹን በጉዳት ምክንያት ወደ ሜዳ ይዞ ያልገባው ሪያል ማድሪድ ጠንካራ ብቃት አሳይቷል። ውጤቱን ተከትሎ የ15 ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ማድሪድ ወደ ሩብ ፍጻሜ የማለፍ እድሉን አስፍቷል። ማንችስተር ሲቲ በመልሱ ጨዋታ ውጤቱን የመቀልበስ ከባድ የቤት ስራ ይጠብቀዋል።   በሌላኛው መርሐ-ግብር የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒኤስጂ ቼልሲን 5 ለ 2 አሸንፏል። በፓርክ ደ ፕሪንስ በተደረገው ጨዋታ ክቪቻ ክቫራትስኬሊያ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ብራድሊ ባርኮላ፣ ኡስማን ደምበሌ እና ቪቲንሃ ቀሪዎቹን ጎሎች ለፈረንሳዩ ክለብ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ማሎ ጉስቶ እና ኢንዞ ፈርናንዴዝ ለቼልሲ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ፒኤስጂ ወደ ሩብ ፍጻሜ የመግባት እድሉን የበለጠ ሰፊ አድርጓል።   ቦዶ ግሊምት ስፖርቲንግ ሊዝበንን 3 ለ 0 አሸንፏል። በአስፕማይራ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኦሌ ብሉምበርግ እና ካስፐር ዋርትስ ሆግ በጨዋታ፣ ሶንድሬ ብሩንስታድ ፌት በፍጹም ቅጣት ምት ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሻምፒዮንስ ሊጉ ጥሩ ግስጋሴ እያደረገው የሚገኘው የኖርዌው ክለብ ቦዶ ግሊምት ወደ ሩብ ፍጻሜ የማለፍ እድሉ ሰፊ ሆኗል። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ባየር ሌቨርኩሰን እና አርሰናል አንድ አቻ ተለያይተዋል። በጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ስድስቱ የእንግሊዝ ክለቦች ማሸነፍ አልቻሉም። የጥሎ ማለፍ የመልስ ጨዋታዎች በቀጣዩ ሳምንት ይደረጋሉ።
የዓለም አትሌቲክስ አህጉራዊ ውድድር መዳረሻ የሆነችው አዲስ አበባ
Mar 11, 2026 80
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2018 (ኢዜአ)፡- የዓለም አትሌቲክስ እ.አ.አ በ2026 አዳዲስ የኮንቲኔንታል ቱር ውድድሮች ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ከነዚህ ውድድሮቹ አንዱ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል።   በመዲናዋ በሚገኘው የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የሚካሄደው ውድድር በዓለም አትሌቲክስ የነሀስ ደረጃ እንደተሰጠው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የዓለም አትሌቲክስን ዋቢ በማድረግ ያወጣው መረጃ ያመለክታል።   ኢትዮጵያ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር የማዘጋጀት እድል አግኝታለች። የዓለም አትሌቲክስ ውድድሮቹን አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የዓለም አትሌቲክስ የነሀስ ደረጃ የተሰጠው ሲሆን ሚያዚያ 10/2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የወጣው መርሐ-ግብር ያመለክታል። ኢትዮጵያ ፣ግብፅ ፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ሌሴቶ፣ ኦማን እና ሳዑዲ አረቢያ የዓለም አትሌቲክስ የ2026 አዳዲስ የኮንቲኔንታል ቱር ውድድሮች ከሚደረግባቸው ሀገራት መካከል ይጠቀሳሉ። ውድድሩ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ አትሌቶች የሚሳተፉበት ከመሆኑ ባሻገር አሸናፊ የሚሆኑ አትሌቶች ከፍተኛ ሽልማት እንደሚያገኙ የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል።
ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ ቀረበ
Mar 11, 2026 110
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳኅሌ ኢትዮጵያ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር ለምታደርገው የ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዝግጅት ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ አቀረቡ። በዚህም መሠረት፤ አቡበከር ኑራ (ከኢትዮጵያ መድን)፣ ፍሬው ጌታሁን (ከድሬዳዋ ከተማ) እና ሰኢድ ሀብታሙ (ከሐዋሳ ከተማ) ጥሪ የተደረገላቸው ግብ ጠባቂዎች ናቸው። እንዲሁም ዓለምብርሃን ይግዛው (ከመቻል)፣ አሥራት ቱንጆ (ከድሬዳዋ ከተማ)፣ ያሬድ ካሳዬ (ከኢትዮጵያ መድን)፣ አብዱሰላም ዩሱፍ (ከድሬዳዋ ከተማ)፣ ያሬድ ባዬ (ከሲዳማ ቡና)፣ ራምኬል ጀምስ (ከኢትዮጵያ ቡና)፣ ምኞት ደበበ (ከፋሲል ከነማ) እና ግሩም ሀጎስ (ከመቻል) ጥሪ የተደረገላቸው የተከላካይ መስመር ተጫዋቾች ናቸው። በአማካይ ክፍል ደግሞ ሀብታሙ ተከስተ (ከፋሲል ከነማ)፣ ጋቶች ፓኖም (ከአል አረቢ ሳዑዲ ዓረቢያ)፣ ብሩክ እንዳለ (ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ)፣ ብዙዐየሁ ሰይፉ (ከአዳማ ከተማ)፣ ወገኔ ገዛኸኝ (ከኢትዮጵያ መድን) እና ቢኒያም ዐይተን (ከአዳማ ከተማ) በጥሪው ተካትተዋል።   በተጨማሪም በአጥቂ መስመር ቸርነት ጉግሳ (ከመቻል)፣ መስፍን ታፈሰ (ከኢትዮጵያ ቡና)፣ አቡበከር ሳኒ (ከአዳማ ከተማ)፣ ከቤ ብዙነህ (ከነገሌ አርሲ)፣ አቤል ያለው (ከሲዳማ ቡና) እና ከነዓን ማርክነህ (ከአል ሻባብ ኦማን) ጥሪ ቀርቦላቸዋል። አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳኅሌ ተጫዋቾቹ ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር በኋላ ዝግጅታቸውን እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል። ተጫዋቾቹን ለመመልመል እና ለመምረጥ ጊዜ ተወስዶ መሠራቱንም አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ጨዋታዋን ሳኦቶሜ የሜዳ ጨዋታዋን ለማድረግ በመረጠችው ሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ታደርጋለች። የመልሱ ጨዋታ ደግሞ በድሬዳዋ ስታዲየም መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከናወን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ አመላክቷል። 36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኬንያ፣ ታንዛንያ እና ዑጋንዳ ጣምራ አዘጋጅነት በፈረንጆቹ ሰኔ 2027 ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የ18ኛ ሳምንት ሁለተኛ ቀን ውሎ 
Mar 11, 2026 76
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከረፋዱ 4 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከአዲስ አበባ ከተማ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሸገር ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው 17 ጨዋታዎች በ11ዱ አሸንፎ በአምስቱ ተሸንፎ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። በ17ቱ ጨዋታዎች 27 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 18 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ34 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው አዲስ አበባ ከተማ በሊጉ 17 ጨዋታዎች አከናውኖ ሁለት ጊዜ ድል ሲቀናው 13 ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። ዘጠኝ ግቦችን ሲያስቆጥር 35 ጎሎችን አስተናግዷል። አዲስ አበባ ከተማ በስምንት ነጥብ የመጨረሻውን 14ኛ ደረጃ ይዟል። መርሐ-ግብሩ ሸገር ከተማ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ አዲስ አባ ከተማ በሊጉ ሶስተኛ ድሉን ለማስመዝገብ የሚያደርጉት ነው።   በሌላኛው መርሐ-ግብር አዳማ ከተማ ከይርጋጨፌ ቡና ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አዳማ ከተማ እስከአሁን በሊጉ ያሸነፋቸው ጨዋታዎች አራት ናቸው። ስምንት ጊዜ ሲሸነፍ አምስት ጊዜ አቻ ወጥቷል። 12 ግቦችን ሲያስቆጥር 27 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ17 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው ይርጋጨፌ ቡና በበኩሉ 17 ጨዋታዎችን አድርጎ ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ በ10ሩ ተሸንፏል። በአምስት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። በጨዋታዎቹ ላይ ስምንት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 25 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አዲስ አዳጊው ይርጋጨፌ ቡና በ11 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። በ17ኛ ሳምንት አዳማ ከተማ ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ይርጋጨፌ ቡና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ3 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ።
ዓለም በጉጉት የሚጠብቀው የሪያል ማድሪድ እና ማንችስተር ሲቲ ተጠባቂ ጨዋታ
Mar 11, 2026 148
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።   ጋላታሳራይ ሊቨርፑልን አሸነፈ በሻምፒዮንስ ሊጉ ባየር ሙኒክ እና አትሌቲኮ ማድሪድ ድል ቀንቷቸዋል ምሽት 5 ሰዓት ላይ ሪያል ማድሪድ ከማንችስተር ሲቲ በበርናባው ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪያንን ቀልብ ስቧል።   ሪያል ማድሪድ በጥሎ ማለፍ ማጣሪያው ቤኔፊካን በድምር ውጤት 3 ለ 1 በማሸነፍ 16 ውስጥ ገብቷል። ማንችስተር ሲቲ በ16 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዞ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅሏል። ሁለቱ ቡድኖች በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ሲገናኙ የአሁኑ ለ16ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም በነበራቸው የ15 ጊዜ ግንኙነት ቡድኖች በተመሳሳይ አምስት ጊዜ አሸንፈዋል። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። ሪያል ማድሪድ በ15ቱ ጨዋታዎች ላይ 26 ግቦችን ሲያስቆጥር ማንችስተር ሲቲ 25 ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ቡድኖቹ ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት እ.አ.አ በ2024/25 የውድድር ዓመት በተመሳሳይ በጥሎ ማለፍ ዙር ላይ ነበር። በወቅቱ ሪያል ማድሪድ በደርሶ መልስ ውጤት 6 ለ 3 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። በአውሮፓ መድረክ ላለፉት ተከታታይ ዓመታት እየተፎካከሩ የሚገኙት ሁለቱ ክለቦች ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ሪያል ማድሪድ 15 ጊዜ ዋንጫውን በማንሳት የውድድሩ ስኬታማ ክለብ ነው። ማንችስተር ሲቲ አንድ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት ሆኗል። የ44 ዓመቱ ጣልያናዊ ማውሪዚዮ ማሪያኒ ተጠባቂውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል።   በሌላኛው መርሐ-ግብር ፒኤስጂ ከቼልሲ ምሽት 5 ሰዓት ላይ በፓርክ ደ ፕሪንስ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ፒኤስጂ የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ነው። ቼልሲ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አንድ ጊዜ አንስቷል። ሁለቱ ክለቦች ጠንካራ ፍልሚያ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።   ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ ባየር ሌቨርኩሰን ከአርሰናል በቤይ አሬና ስታዲየም ይጫወታሉ። የጀርመኑ ባየር ሌቨርኩሰን በጥሎ ማለፍ ማጣሪያው የግሪኩን ኦሎምፒያኮስን በደርሶ መልስ 2 ለ 0 በማሸነፍ ጥሎ ማለፍ ገብቷል። አርሰናል በውድድሩ የሊግ ምዕራፍ ያደረጋቸውን ስምንት ጨዋታዎች በማሸነፍ በ24 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ የሚታወስ ነው።   ቦዶ ግሊምት ከስፖርቲንግ ሊዝበን ምሽት 5 ሰዓት ላይ በአስፕማይራ ስታዲየም ይጫወታሉ። የኖርዌው ቦዶ ግሊምት በጥሎ ማለፍ ማጣሪያው ኢንተር ሚላንን በድምር ውጤት 5 ለ 2 አሸንፏል። የፖርቹጋሉ ስፖርቲንግ ሊዝበን በ16 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዞ በቀጥታ ጥሎ ማለፉን መቀላቀሉ ይታወቃል።
በሻምፒዮንስ ሊጉ ባየር ሙኒክ እና አትሌቲኮ ማድሪድ ድል ቀንቷቸዋል
Mar 11, 2026 124
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ሶስት ጨዋታዎች ተደርገዋል። ጋላታሳራይ ሊቨርፑልን አሸነፈ ሐዋሳ ከተማ ወሳኝ ድል አሳክቷል በቤርጋሞ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ባየር ሙኒክ አተላንታን 6 ለ 1 ረትቷል።   ማይክል ኦሊሴ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ጀማል ሙሲያላ፣ ኒኮላስ ጃክሰን፣ ሰርጌ ናብሪ እና ጆሲፕ ስታኒሲች ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ማሪዮ ፓሳሊች ለአተላንታ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው ባየር ሙኒክ ፍጹም የበላይነት ወስዷል። የጀርመኑ ኃያል ክለብ ወደ ሩብ ፍጻሜ የማለፍ እድሉ እጅጉን የሰፋ ሆኗል።   በሌላኛው መርሐ-ግብር አትሌቲኮ ማድሪድ ቶተንሃም ሆትስፐርስን 5 ለ 2 አሸንፏል። በዋንዳ ሜትሮፓሊታኖ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጁሊያን አልቫሬዝ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ አንቶዋን ግሪዝማን፣ ማርኮስ ሊዮሬንቴ እና ሮቢን ለኖርማንድ ቀሪዎቹን ጎሎች አስቆጥረዋል። ፔድሮ ፖሮ እና ዶምኒክ ሶላንኬ ለቶተንሃም ጎሎቹን ከመረብ ጋር አገናኝተዋል። በጨዋታው አትሌቲኮ ማድሪድ ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል። በውጤት ማጣት ቀውስ ውስጥ የሚገኘው ቶተንሃም ደካማ እንቅስቃሴ አሳይቷል። የማድሪዱ ክለብ ወደ ሩብ ፍጻሜ የማለፍ እድሉን አስፍቷል።   በሴንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኒውካስል ዩናይትድ እና ባርሴሎና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ሃርቪ ባርንስ በ86ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ኒውካስትልን መሪ አድርጓል። ጨዋታው በኒውካስትል አሸናፊነት ተጠናቀቀ ሲባል ላሚን ያማል በ96ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ለባርሴሎና የአቻነቷን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ጨዋታው ተመጣጣኝ እና አዝናኝ ፉክክር ተደርጎበታል። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ጋላታሳራይ ሊቨርፑልን 1 ለ 0 አሸንፏል። የመልስ ጨዋታዎች በቀጣይ ሳምንት ይካሄዳሉ።
ሐዋሳ ከተማ ወሳኝ ድል አሳክቷል
Mar 10, 2026 136
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት ሐዋሳ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታን 1 ለ 0 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ፤ አምበሉ ሽመልስ በቀለ በ75ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከሶስት የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሐዋሳ ከተማ በ40 ነጥብ ደረጃውን ከሶስተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ማድረግ ችሏል። በውድድር ዓመቱም 11ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ዘጠነኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቀሌ 70 እንደርታ በ22 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም።   በሌላኛው ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ናይጄሪያዊው ጄሮም ፍሊፕ እና አብዱልራህማን መሐመድ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ ሶስተኛ ድሉን ያስመዘገበው አርባምንጭ ከተማ በ19 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ላለመውረድ በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በውድድር ዓመቱ አራተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አዳማ ከተማ በ33 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። አዳማ ከተማ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ድል አልቀናውም። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 23ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ24ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ከመጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
ኢትዮ ኤሌክትሪክ መሪነቱን ያጠናከረበት ወሳኝ ድል አስመዘገበ
Mar 10, 2026 96
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1 /2018 (ኢዜአ)፦‎ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ልደታ ክፍለ ከተማን 4 ለ 2 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ዳግማዊት ሰለሞን ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርታለች። ማህሌት ምትኩ ቀሪዋን ጎል ለኢትዮ ኤሌክትሪክ ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ሄለን ጌታቸው እና ይታገሱ ተገኘወርቅ ለልደታ ክፍለ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሀትሪክ የሰራችው ዳግማዊት ሰለሞን የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። በሊጉ 16ኛ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ49 ነጥብ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል። ከተከታዩ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ያለው ልዩነት በሁለት ነጥብ ቀጥሏል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 11ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ልደታ ክፍለ ከተማ በ15 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። የኢትዮ ኤሌክትሪኳ አጥቂ ዳግማዊት ሰለሞን በሊጉ ያስቆጠረቻቸውን ግቦች ወደ 22 ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቷን አጠናክራለች። ዛሬ በተደረገ የ18ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቦሌ ክፍለ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም