ስፖርት - ኢዜአ አማርኛ
ስፖርት
በተጠባቂው ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ከቶተንሃም ሆትስፐርስ ጋር አቻ ተለያየ
Feb 1, 2026 54
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐ-ግብር ቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ማንችስተር ሲቲ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን በማሸነፍ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ ማምሻውን በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ራያን ቸርኪ በ11ኛው እና አንቶዋን ሴሜንዮ በ44ኛው ደቂቃ ባስቆጠሯቸው ግቦች ማንችስተር ሲቲ 2 ለ 0 መምራት ችሎ ነበር። ከእረፍት መልስ ዶምኒክ ሶላንኬ በ53ኛው እና በ71ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋቸው ግቦች ቶተንሃምን አቻ አድርጓል። በመጀመሪያው አጋማሽ ማንችስተር ሲቲ፣ በሁለተኛው አጋማሽ ቶተንሃም ሆትስፐርስ የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገዋል። የ2 ለ 0 መሪነቱን ማስጠበቅ ያልቻለው ማንችስተር ሲቲ በ47 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ጥሏል። ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ከአራት ወደ ስድስት ከፍ ብሏል። ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ29 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ የዛሬውን ጨምሮ ባለፉት ስድስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ዛሬ በተደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን 3 ለ 2 ሲያሸንፍ ብሬንትፎርድ አስቶንቪላን 1 ለ 0 ረቷል። ኖቲንግሃም ፎረስት እና ክሪስታል ፓላስ አንድ አቻ ተለያይተዋል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ነገ ሰንደርላንድ እና በርንሌይ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል።
ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሶስተኛ ከፍ አደረገ
Feb 1, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ18ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ከቤ ብዙነህ በጨዋታ እና ዳዊት ተፈራ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ነገሌ አርሲ በ32 ነጥብ ደረጃውን ከአራተኛ ወደ ሶስተኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ዘጠነኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በሊጉ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ20 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ተጠባቂ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 አሸንፏል። የቅዱስ ጊዮርጊሱ ቶሎሳ ንጉሴ በ82ኛው ደቂቃ በራሱ ላይ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በውድድር ዓመቱ ስምንተኛ ድሉን ያስመዘገበው ፋሲል ከነማ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ32 ነጥብ ከነበረበት አምስተኛ ደረጃ ወደ አራተኛ ከፍ ብሏል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ለሰባተኛ ጊዜ የተሸነፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ23 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት ሶስት ተከታታይ ጨዋታዎች አላሸነፈም። በሌላኛው መርሐ-ግብር መቀሌ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። የኢትዮጵያ ቡናው በፍቃዱ አለማየሁ በራሱ ላይ ለመቀሌ 70 እንደርታ፣ አምበሉ ራምኬል ጀምስ ለኢትዮጵያ ቡና ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። መቀሌ 70 እንደርታ በ18 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ኢትዮጵያ ቡና በ20 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ቀን ላይ በተደረገ የመጀመሪያ ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 በመርታት በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 18ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ19ኛ ሳምንት እና የሊጉ የመጀመሪያ ዙር የማጠናቀቂያ መርሐ-ግብር ከጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን በማሸነፍ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ
Feb 1, 2026 57
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በ24ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን 3 ለ 2 በመርታት ደረጃውን ከነበረበት ወደ አራተኛ ከፍ ያደረገ ሲሆን ሶስተኛ ተከታታይ ድሉንም አስመዝግቧል። የማንችስትር ዩናይትድን ግቦች ካስሚሮ በ19ኛው፣ ኩና በ56ኛው እንዲሁም ሴስኮ በ94ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፈዋል። በአንጻሩ ሂምኔዝ በ85ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት እና ኬቪን በ92ኛው ደቂቃ በጨዋታ ለፉልሃም ግቦችን አስቆጥረዋል። ውጤቱን ተከትሎም ማንችስተር ዩናይትድ በ41 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ዳግም የተረከበ ሲሆን፤ ፉልሃም በ34 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሌላ የጨዋታ መርሐ-ግብር ብሬንትፎርድ አስቶንቪላን በሜዳው 1 ለ 0 ሲያሸንፍ፤ ኖቲንግሃም ከክሪስታል ፓላስ አንድ አቻ ተለያይተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
Feb 1, 2026 50
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በ18ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 ረትቷል። 10 ሠዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ፤ ፋሲል ከነማ የቅዱስ ጊዮርጊሱ ቶሎሳ ንጉሴ በራስ ላይ ባስቆጠራት ግብ አሸናፊ ሆኗል። ቀደም ብሎ 9 ሠዓት ላይ በተካሄደው የዕለቱ መርሐ-ግብር መቀሌ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ ቡና አንድ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል።
መቀሌ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ ቡና አቻ ተለያዩ
Feb 1, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በ18ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የተገናኙት መቀሌ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ ቡና አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም ተካሂዷል። በጨዋታው ላይ የኢትዮጵያ ቡናው ራምኬል ጀምስ በ19ኛው ደቂቃ ኢትዮጵያ ቡናን መሪ ያደረች ግብ ማስቆጠር ችሏል። እንዲሁም በ31ኛው ደቂቃ በፍቃዱ ዓለማየሁ (በራስ ላይ) ግብ በማስቆጠሩ ተከትሎ መቀሌ 70 እንደርታ አቻ የወጣበትን ዕድል አግኝቷል።
አርባምንጭ ከተማ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዘገበ
Feb 1, 2026 51
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ18ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር አርባምንጭ ከተማ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ታምራት እያሱ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥሯል። ፍሬው ሰለሞን ለወልዋሎ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ድሉን ያስመዘገበው አርባምንጭ ከተማ በ11 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። በአንጻሩ በሊጉ ስምንተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ16 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል።
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የነገሱበት የዱባይ ማራቶን
Feb 1, 2026 77
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ ዛሬ ማለዳ በተካሄደው 25ኛው የዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸንፈዋል። በወንዶች አትሌት ንብረት መላክ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ00 ሴኮንድ አንደኛ ወጥቷል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ያሲን ሃጂ ሁለተኛ እና ሩዋንዳዊው ጆን ሃኪዚማና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ4ኛ እስከ 10ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል። በሴቶች አንቺንአሉ ደሴ 2 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ31 ሴኮንድ አሸንፋለች። ሙሉዬ ደቀቦ እና ፋንቱ ወርቁ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንደኛ እስከ 10ኛ ደረጃን በመያዝ በበላይነት አጠናቀዋል። በሁለቱም ጾታዎች ያሸነፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተመሳሳይ የ80 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የውድድሩ አዘጋጅ አካል በአጠቃላይ ለአትሌቶች ከ336 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ ሽልማት መስጠቱን አስታውቋል። እ.አ.አ በ1998 የተጀመረው የዱባይ ማራቶን በዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ የተሰጠው የጎዳና ላይ ውድድር ነው።
በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
Feb 1, 2026 62
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት ዛሬ በሚደረጉ ጨዋታዎች ይጠናቀቃል። ከቀኑ 10 ሰዓት ፋሲል ከነማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። ፋሲል ከነማ በሊጉ ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በሰባቱ አሸንፎ በአንዱ ተሸንፎ በስምንቱ አቻ ወጥቷል። በ16ቱ ጨዋታዎች 13 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 7 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ፋሲል ከነማ በ29 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ፋሲል ከነማ በዘንድሮው የውድድር ዓመት አነስተኛ ሽንፈት ያስተናገደ እና ዝቅተኛ የግብ መጠን የተቆጠረበት ቡድን ነው። ተጋጣሚው ቅዱስ ጊዮርጊስ በሊጉ 17 ጨዋታዎች አከናውኖ ስድስት ጊዜ ድል ሲቀናው በስድስቱ ተሸንፏል። አምስት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። 15 ግቦችን ሲያስቆጥር 12 ጎሎችን አስተናግዷል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ23 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። መርሐ-ግብሩ ፋሲል ከነማ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሁለት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። በሌላኛው መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከነገሌ አርሲ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እስከ አሁን በሊጉ ማሸነፍ የቻለው ጨዋታ ብዛት አራት ብቻ ነው። አምስት ጊዜ ሲሸነፍ ስምንት ጊዜ አቻ ወጥቷል። 20 ግቦችን ሲያስቆጥር በተመሳሳይ 20 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ20 ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው ነገሌ አርሲ በበኩሉ 17 ጨዋታዎችን አድርጎ ስምንት ጊዜ ሲያሸንፍ አራት ጊዜ ተሸንፏል። በአምስት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 18 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 12 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ነገሌ አርሲ በ29 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። በ17ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮጵያ ቡናን፣ ነገሌ አርሲ የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፈዋል። ሁለቱም ቡድኖች በድል ጉዞ ለመቀጠል የሚያደርጉት ጨዋታ ተመጣጣኝ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ መቀሌ 70 እንደርታ ከኢትዮጵያ ቡና በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። መቀሌ 70 እንደርታ በ17 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ኢትዮጵያ ቡና በ19 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። በ17ኛ ሳምንት መቀሌ 70 እንደርታ ከአዳማ ከተማ ጋር ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ኢትዮጵያ ቡና ባለፉት ሶስት የሊጉ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ጨዋታው ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከአርባምንጭ ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ16 ነጥብ 19ኛ እና አርባምንጭ ከተማ በስምንት ነጥብ 20ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛሉ። ወልዋሎ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። በሊጉ እስከ አሁን ምንም ጨዋታ ማሸነፍ ያልቻለው ብቸኛው ክለብ አርባምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ሶስት ነጥቡን ለማግኘት ይጫወታል።
በሊጉ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከማንችስተር ሲቲ ማንችስተር ዩናይትድ ከፉልሃም የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Feb 1, 2026 73
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከማንችስተር ሲቲ በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየም ይጫወታሉ። ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ28 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ማንችስተር ሲቲ በ46 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች ከድል የራቀው ቶተንሃም ሆትስፐርስ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ተጋጣሚው ማንችስተር ሲቲ የዛሬው ጨዋታ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ እና ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ዝቅ ለማድረግ ያስችለዋል። በሌላኛው መርሐ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከፉልሃም ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታውን በኦልትራፎርድ ስታዲየም ጨዋታውን ያደርጋል። ማንችስተር ዩናይትድ በ38 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ፉልሃም በ34 ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። በጊዚያዊ አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ እየተመራ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች የሊጉን መሪ አርሰናል እና ተከታዩን ማንችስተር ሲቲ ያሸነፈው ዩናይትድ በጥሩ መነቃቃት ላይ ይገኛል። የዛሬውንም ጨዋታ የማሸነፍ ግምት አግኝቷል። ሶስት ነጥብ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ነው። በ23 ሳምንት ብራይተንን ያሸነፈው ተጋጣሚው ፉልሃም ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። በቪላ ፓርክ ስታዲየም አስቶንቪላ ከብሬንትፎርድ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። አስቶንቪላ በ46 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ብሬንትፎርድ በ33 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ማሸነፍ አስቶንቪላን በዋንጫ ፉክክሩ ላይ እንዲቆይ ያደርገዋል። ተጋጣሚው ብሬንትፎርድ ከሁለት ተከታታይ ሽንፈቶች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ኖቲንግሃም ፎረስት ከክሪስታል ፓላስ ከቀኑ 11 ሰዓት በሲቲ ግራውንድ ስታዲየም ይጫወታሉ።
ሊቨርፑል ወደ አሸናፊነት ተመልሷል
Feb 1, 2026 77
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት ሊቨርፑል ኒውካስትል ዩናይትድን 4 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሁጎ ኢኪቲኬ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ፍሎሪያን ዊትዝ እና ኢብራሂማ ኮናቴ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኢኪቲኬ የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተመርጧል። በቅርቡ አባቱን በሞት ያጣው ኢብራሂማ ኮናቴ ግብ ካስቆጠረ በኋላ በእንባ ስሜቱን ገልጿል። አንቶኒ ጎርደን ለኒውካስትል ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከአምስቱ የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሊቨርፑል በ39 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ቀያዮቹ እ.አ.አ በ2026 የመጀመሪያ የሊግ ድላቸውን አግኝተዋል። ሊቨርፑል በውድድር ዓመቱ 11ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በሊጉ ዘጠነኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኒውካስትል ዩናይትድ በ33 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል።
ቼልሲ ዌስትሃም ዩናይትድን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ አራተኛ ከፍ አደረገ
Jan 31, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት ቼልሲ ከመመራት ተነስቶ ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 2 አሸንፏል። አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከባህርዳር ከተማ ጋር አቻ ተለያየ ማምሻውን በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጃሮድ ቦውን በ7ኛው እና ክሪሴንሲዮ ሳመርቪል በ36ኛው ደቂቃ ባስቋጠሯቸው ግቦች ዌስትሃም ዩናይትድ 2 ለ 0 መምራት ችሎ ነበር። ጆአኦ ፔድሮ በ57ኛው፣ ማርክ ኩኩሬላ በ70ኛው እና ኢንዞ ፈርናንዴዝ በ92ኛው ደቂቃ ያስቆጠሯቸው ግቦች ቼልሲን አሸናፊ አድርጓል። የዌስትሃም ዩናይትዱ ተከላካይ ጂን-ክሌር ቶዲቦ በ101ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። በሊጉ 11ኛ ድሉን ያስመዘገበው ቼልሲ በ40 ነጥብ ደረጃውን ከአምስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። የሁለት ግብ መሪነቱን አሳልፎ የሰጠው ዌስትሃም ዩናይትድ በ20 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በውድድር ዓመቱም 14ኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል።
የኦሮሚያ ክልል ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የተሰራው ስራ ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል
Jan 31, 2026 105
አዳማ፤ ጥር 23/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የተሰራው ስራ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ ገለጹ። አዳማ የስምጥ ሸለቆ የቱሪስት ከተማ መሆኗን ለማስተዋወቅ ያለመ የከተማዋ ነዋሪዎች የተሳተፉበት የምሽት የታላቁ ሩጫ ውድድው ተካሄዷል። በሩጫው ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ በክልሉ የተከናወኑ የከተሞች ልማት ስራዎች ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ ማድረግ አስችሏል ብለዋል። በተለይም በክልሉ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ከተሞችን ተመራጭ የቱሪስት መደረሻ እንዲሁም የኢንቨስትመንት ማዕከል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ከተሞች ውብ፣ ጽዱ እና ምቹ እየሆኑ መምጣታቸው የህብረተሰቡን የአኗኗር ዘይቤ ለመለወጥ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ረገድ በጎ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ጠቅሰዋል። አዳማ በተሻለ መልኩ የከተማ ልማት ስራዎች ከተከናወነባቸው ከተሞች መካከል አንዷ መሆኗን ጠቅሰው ከተማዋ ወደ ዘመናዊ ከተማነት እየተሸጋገረች መሆኑንም አስረድተዋል። በዚሁ መነሻነት ለመጀመሪያ ጊዜ የከተሞችን የኮሪደር ልማት ለማስተዋወቅና የቱሪስት ፍሰቱን ለማሳደግ ያለመ የምሽት የሩጫ መርሃ ግብር ዛሬ መካሄዱን ተናግረዋል። የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው የአዳማ ከተማን ለነዋሪቿ ምቹ ለማድረግ እንዲሁም የኢንዱስትሪ ማእከል እንድትሆን በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል። በቀጣይም ከተለመደው መንገድ በመውጣትና ሌት ከቀን በመስራት የከተማዋን ዘመናዊነት እና እድገት የሚያፋጥኑ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል። በከተማዋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን ለማሳካት ፍጥነትና ጥራት ወሳኝ ነው ያሉት አቶ ሃይሉ ለዚህም ህዝቡ የጀመረውን ድጋፍ ማጠናከር አለበት ብለዋል። የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ነጋ ወዳጆ በበኩላቸው ቱሪዝም የከተሞችን እድገት ከማፋጠን ባለፈ አንድነት እና ህብረትን ያጠናክራል ብለዋል። ዛሬ በአዳማ ከተማ የተካሄደው የምሸት ሩጫ ከተማዋን የበለጠ በማስተዋወቅ ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን የላቀ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ገልጸዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የኦሮሚያ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ፣ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ፣ የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ቢያንን ጨምሮ ሌሎች የክልሉና የከተማ መስተደድሩ አመራሮችና የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ
Jan 31, 2026 84
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል። ማምሻውን በኢላንድ ሮድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማርቲን ዙቢሜንዲ፣ ቪክቶር ዮኮሬስ፣ ጋብርኤል ጄሱስ እና የሊድስ ዩናይትዱ ግብ ጠባቂ ካርል ዳርሎው በራሱ ላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው አርሰናል በ53 ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት በጊዜያዊነት ወደ ሰባት ከፍ አድርጓል። መድፈኞቹ በሊጉ 16ኛ ድላቸውን አስመዝግበዋል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሊድስ ዩናይትድ በ26 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። በሌሎች መርሐ-ግብሮች ቦርንማውዝ ዎልቭስን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ፣ ብራይተን እና ኤቨርተን አንድ አቻ ተለያይተዋል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከባህርዳር ከተማ ጋር አቻ ተለያየ
Jan 31, 2026 66
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት ሲዳማ ቡና እና ባህርዳር ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም መስፍን ታፈሰ በ61ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል ሲዳማ ቡና መሪ ሆኗል። ከእረፍት መልስ ሰቲህ ኦሴ በ71ኛው ደቂቃ የባህር ዳር ከተማን የአቻነት ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ነጥቡን ወደ 34 ከፍ አድርጓል። ከተከታዩ ሀዋሳ ከተማ ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ከአራት ወደ ሁለት ዝቅ ብሏል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አላሸነፈም። ባህርዳር ከተማ በ22 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ባህርዳር ከተማ ለ11ኛ ጊዜ አቻ በመውጣት በሊጉ በበርካታ ጨዋታዎች አቻ የወጣ ቡድን ሆኗል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው መርሐ-ግብር ሸገር ከተማ መቻልን 1 ለ 0 አሸንፏል። ቡልቻ ሹራ በ59ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ከስምንት የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሸገር ከተማ በ20 ነጥብ ደረጃውን ከ16ኛ ወደ 13 ከፍ አድርጓል። በሊጉ አራተኛ ድሉን አስመዝግቧል። ከሶስት ተከታታይ ጨዋታዎች በኋላ ሽንፈት ያስተናገደው መቻል በ29 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። በውድድር ዓመቱ ያስተናገደው ሽንፈት ብዛት አምስት ደርሷል። ቀን ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 0 አሸንፏል።
ድሬዳዋ ከተማ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል
Jan 31, 2026 72
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት ድሬዳዋ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ መሐመድኑር ናስር በ64ኛው እና በ71ኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ድሬዳዋ ከተማ በ23 ነጥብ ደረጃውን ከ13ኛ ወደ 9ኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ለሰባተኛ ጊዜ የተሸነፈው ሀድያ ሆሳዕና በ20 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከባህርዳር ከተማ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Jan 31, 2026 112
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በተጠባቂው ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሁለተኛ ከፍ አደረገ ወላይታ ድቻ እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋሩ ከመርሐ-ግብሮቹ መካከል ሲዳማ ቡና ከባህርዳር ከተማ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ ካከናወናቸው 17 ጨዋታዎች መካከል ዘጠኙን ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪው ስድስት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 23 ግቦችን ሲያስቆጥር 9 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ33 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። በሊጉ ካደረጋቸው 17 ጨዋታዎች መካከል አራቱን ያሸነፈው ባህርዳር ከተማ በበኩሉ ሶስት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በ10 ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 11 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 10 ግቦች ተቆጥረውበታል። ባህርዳር ከተማ በ22 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቡድኑ በሊጉ ለበርካታ ጊዜ አቻ የወጣ ቡድን ነው። ሲዳማ ቡና በ17ኛ ሳምንት በነገሌ አርሲ ካስተናገደው ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ድል ከቀናው ከተከታዩ ሐዋሳ ከተማ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ነጥብ ከፍ ያደርጋል። በሌላ በኩል ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ መቻል ከሸገር ከተማ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። መቻል በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው 17 ጨዋታዎች በስምንቱ ድል ሲቀናው አራት ጊዜ ተሸንፏል። በአምስት ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። 23 ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ 13 ግቦች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ29 ነጥብ ሶስተኛ ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው ሸገር ከተማ በበኩሉ በሊጉ 17 ጨዋታዎችን በማድረግ ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ በስድስቱ ተሸንፏል። ስምንት ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 13 ግቦችን ሲያስቆጥር 17 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በ17 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ያሸነፈው መቻል በድል ጉዞው ለመቀጠል ይፋለማል። ካሸነፈ በድጋሚ ወደ ሁለተኛ ደረጃ ይመለሳል። በአንጻሩ ባለፉት ስምንት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ከድል የራቀው ሸገር ከተማ ማሸነፍ ከወራጅ ቀጠና በመጠኑም ቢሆን የሚርቅበትን እድል ይሰጠዋል። እንዲሁም ድሬዳዋ ከተማ ከሀዲያ ሆሳዕና ከቀኑ 7 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ድሬዳዋ ከተማ በ20 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ሲይዝ ሀዲያ ሆሳዕና በተመሳሳይ 20 ነጥብ በግብ ክፍያ በልጦ 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ባለፉት ስድስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ያላሸነፈው ድሬዳዋ ከተማ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። በ17ኛ ሳምንት በወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሽንፈት ያስተናገደው ሀዲያ ሆሳዕና ማሸነፍ ወደ ድል መንገድ ይመልሰዋል።
የሊጉ መሪ አርሰናል ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ይጫወታል
Jan 31, 2026 132
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል። የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ መርሐ-ግብር ይፋ ሆነ በዕለቱ አምስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ሊድስ ዩናይትድ የሊጉን መሪ አርሰናል ምሽት 12 ሰዓት ላይ በኢላንድ ሮድ ስታዲየም ያስተናግዳል። የዮርክሻየሩ ሊድስ ዩናይትድ በ26 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። የሰሜን ለንደኑ አርሰናል በ50 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ባለሜዳው ሊድስ በውድድር ዓመቱ 23 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ ዘጠኝ ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ ስምንት ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው አርሰናል በሊጉ ካከናወናቸው 23 ጨዋታዎች መካከል በ15ቱ ድል ሲቀናው በሶስቱ ተሸንፏል። በአምስቱ ጨዋታዎች ላይ ነጥብ ተጋርቷል። ሊድስ ዩናይትድ የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈ ከወራጅ ቀጠና ክልል በመጠኑም ቢሆን እንዲርቅ ያደርገዋል። ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው አርሰናል ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። መድፈኞቹ ካሸነፉ ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያላቸውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ከፍ ማድረግ ያስችላቸዋል። በሌሎች መርሐ-ግብሮች ቼልሲ ከዌስትሃም ዩናይትድ ምሽት 2 ሰዓት ከ30፣ ሊቨርፑል ከኒውካስትል ዩናይትድ ምሽት አምስት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ብራይተን ከኤቨርተን እና ዎልቭስ ከቦርንማውዝ በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
ወላይታ ድቻ እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋሩ
Jan 30, 2026 96
አዲስ አበባ፤ ጥር 22/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ18ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ወላይታ ድቻ እና አዳማ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቴዎድሮስ ኃይለማርያም በ41ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ ወላይታ ድቻ መሪ ሆኗል። ከእረፍት መልስ አቤነዘር ሲሳይ በ69ኛው የአዳማ ከተማን የአቻነት ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ ወላይታ ድቻ በ16 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት ስምንት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። አዳማ ከተማ በ28 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። ዛሬ በተጀመረው 18ኛ ሳምንት ቀን ላይ በተደረጉ ጨዋታዎች ሃዋሳ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ምድረ ገነት ሽሬ እና ኢትዮጵያ መድን ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
በተጠባቂው ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሁለተኛ ከፍ አደረገ
Jan 30, 2026 103
አዲስ አበባ፤ ጥር 22/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ18ኛ ሳምንት የመጀመሪያ መርሐ-ግብር ሃዋሳ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ተባረክ ሄፋሞ በ49ኛው እና ጌታነህ ከበደ በ93ኛው ደቂቃ ላይ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በውድድር ዓመቱ ዘጠነኛ ድሉን ያስመዘገበው ሃዋሳ ከተማ በ32 ነጥብ ከነበረበት ሶስተኛ ደረጃ ወደ ሁለተኛ ከፍ ብሏል። ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት በጊዜያዊነት ወደ አንድ ዝቅ አድርጓል። በአንጻሩ በሊጉ አራተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ26 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች አላሸነፈም። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው ጨዋታ ምድረ ገነት ሽሬ እና ኢትዮጵያ መድን ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። ምድረ ገነት ሽሬ በ22 ነጥብ 10ኛ፣ ኢትዮጵያ መድን በ19 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዘዋል። ምድረ ገነት ሽሬ ባለፉት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በበኩሉ ባለፉት አራት ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ምሽት 12 ሰዓት ላይ የተጀመረው የወላይታ ድቻ እና አዳማ ከተማ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል።
የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ መርሐ-ግብር ይፋ ሆነ
Jan 30, 2026 120
አዲስ አበባ፤ ጥር 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ ተጋጣሚዎች ዛሬ በወጣ ድልድል ተለይተዋል። በዚሁ መሰረት ቤኔፊካ ከሪያል ማድሪድ፣ ሞናኮ ከወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒኤስጂ፣ ካራባግ ከኒውካስትል ዩናይትድ፣ ጋላታሳራይ ከጁቬንቱስ፣ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ከአትላንታ፣ ክለብ ብሩዥ ከአትሌቲኮ ማድሪድ፣ ቦዶ ግሊምት ከኢንተር ሚላን እና ኦሎምፒያኮስ ከባየር ሌቨርኩሰን ይጫወታሉ። የጥሎ ማለፍ ማጣሪያዎቹ በየካቲት ወር የሚካሄዱ ሲሆን በደርሶ መልስ ያሸነፉ ክለቦች ጥሎ ማለፉን ይቀላቀላሉ። በማጣሪያው የሚሳተፉት ክለቦች በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አዲሱ የውድድር ፎርማት ከ9ኛ እስከ 24ኛ ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ ናቸው። ከ36 ክለቦች መካከል በስምንት ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ስምንት ቡድኖች በቀጥታ ወደ ጥሎ ማለፉ ገብተዋል። አርሰናል፣ ባየር ሙኒክ፣ ሊቨርፑል፣ ባርሴሎና፣ ማንችስተር ሲቲ፣ ቼልሲ፣ ቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ስፖርቲንግ ሊዝበን በቀጥታ ጥሎ ማለፉን የተቀላቀሉ ቡድኖች ናቸው።