አርእስተ ዜና
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደህንነትን በማረጋገጥ ለግንባታው አስተዋጽኦ እያደረግን ነው - የመከላከያ ሠራዊት አመራሮችና አባላት
Jun 14, 2025 73
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ደህንነትን በማረጋገጥ ለግንባታው በተለያየ መልኩ አስተዋጽኦ እያደረገን ነው ሲሉ የመከላከያ ሠራዊት አመራሮችና አባላት ገለጹ። የመላው ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት ታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ደረጃ ላይ መድረሱ እንዳስደሰታቸውም ተናግረዋል። በምዕራብ ዕዝ የ404 ሕዳሴ ኮር ሶስተኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን "ሕዳሴን በሕዳሴ ኮር" በሚል መሪ ሐሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች በማክበር ላይ ይገኛል። የሠራዊቱ አባላትም በዛሬው ዕለት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም የመላው ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ደረጃ ደርሶ በመመልከታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።   የምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ሙላቱ ጀልዴ በጉብኝቱ ወቅት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ደረጃ ለመድረሱ መላው ኢትዮጵያውያን ያላሰለሰ ጥረት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። መከላከያ ሠራዊቱ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እውን እንዲሆን የግድቡን ደህንነት ከማስጠበቅ ጀምሮ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸዋል።   በምዕራብ ዕዝ የሪጅን ሶስት ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ዘመኮንን አበራ እንደገለጹት፤ ሠራዊቱ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ግዳጁን በብቃት ለመወጣት ከምን ጊዜውም በላይ ዝግጁ ነው። ሕዳሴ ኮር የግድቡን አካባቢ ሰላምና ጸጥታ ለማስከበር እያደረገ ያለውን ተግባር በውጤታማነት እየተወጣ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህንን ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   በምዕራብ ዕዝ የ403 ኮር አባል ሌተናል ኮሎኔል ፍሰሃ ጥላሁን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የታላቁ የህዳሴ ግድብ የመላው ኢትዮጵያውያን እስትንፋስ በመሆኑ ሠራዊቱ ሁሌም የአካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ታላቁ የሕደሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ ሠራዊቱ አስፈላጊውን ሁሉ ማበርከቱን ጠቁመዋል። ዛሬ ለደረሰበት የመጠናቀቅ ደረጃ ደርሶ በመመልከታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።   በምዕራብ ዕዝ የ403 ኮር አባል ሌተናል ኮሎኔል ቴዎድሮስ ዘመነ እንዳሉትም፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የይቻላል መንፈስ ማሳያ ነው። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ለሀገር በረከት የመሆን ደረጃ ላይ በመድረሱ መደሰታቸውን ጨምረው ተናግረዋል።
ሴቶች በኮንስትራክሽን ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ ነው
Jun 14, 2025 46
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ ሴቶች በኮንስትራክሽን ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን አስታወቀ። ኮርፖሬሽኑ ”ኢትዮጵያ ትገንባ” በሚል መሪ ሀሳብ ሴቶች በኮንስትራክሽን ዘርፉ ያላቸው ተሳትፎ ማዳበር በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ የሚመክር ኮንፍረንስ ተካሂዷል።   በመድረኩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሴት አመራሮች እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ፅህፈት ቤት ሃላፊ ቤዛዊት ግርማ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያ ሴቶች በተለያዩ የግንባታ ፕሮጀክቶችና መሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎች ጉልህ ሚና እየተወጡ ይገኛሉ። በአሁኑ ወቅትም ዘርፉ በቴክኖሎጂ እያደገ በመምጣቱ በአገሪቱ የልማት ጉዞ ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። ኮርፖሬሽኑ በተለያዩ ህጎች ላይ ማሻሻያዎችን በማድረግና ስትራቴጂዎችን በመንደፍ ሴቶች በዘርፉ ያላቸውን ተሳትፎ ከፍ ለማድግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ሴቶች በግንባታ ዘርፍ ያለውን እድልና ቴክኖሎጂ በመጠቀም እውቀታቸውንና ክህሎታቸውን በማዳበር ወደ ዘርፉ በስፋት መግባት እንዳለባቸውም አስታውቀዋል። ሴቶች በኮንስትራክሽን ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ነው ዶክተር ቤዛዊት ያስታወቁት።   የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ፍቅር አባይ በዚሁ ግዜ በአገሪቱ በሚከናወኑ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል ። ይህንንም ለማጠናከር የህግና ፖሊሲ ክፍተቶች ከመሙላት አኳያ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልገው ጠቁመዋል።   በኮንስትራክሽን ስራ ላይ የተሰማሩ መንግስታዊና የግል ድርጅቶችም የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ወሳኝ ድርሻ አላቸው ያሉት ደግሞ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ነጭቴ ፍላቴ ናቸው። የሴቶችን እኩል ተሳታፊነት የተመለከቱ ረቂቅ አዋጆች ፀድቀው ወደ ስራ እንዲገቡ የድርሻቸው እንደሚወጡም ተናግረዋል።   ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና በመድረኩ ጥናት ያቀረቡት ደጅይጥኑ አለነ እንዳሉት ሴቶችን በኮንስትራክሽን ዘርፍ ያላቸው ተሳትፎ ለማሳደግ አቅዶ መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል። በሀገሪቱ እየተከናወኑ በሚገኙ የኮሪደር ልማት የሴቶች ተሳትፎ የተሻለ በመሆኑ ይህም ለሌሎች ዘርፎች ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።    
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በበይነ መረብ ለመፈተን የሚያስችል በቂ ልምምድ አድርገናል-በአዲስ አበባ ተፈታኝ ተማሪዎች
Jun 14, 2025 46
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በበይነ መረብ ለመፈተን የሚያስችል በቂ ልምምድና ዝግጅት ማድረጋቸውን በአዲስ አበባ የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪዎች ተናገሩ፡፡ በአዲስ አበባ ለተፈታኝ ተማሪዎች በበይነ መረብ ለሚሰጠው ፈተና የመጨረሻ የልምምድ ፈተና ዛሬ ተሰጥቷል፡፡   የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በዚሁ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ ትምህርት ቤቶች የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች እንደተናገሩት በበይነ መረብ ለሚሰጠው ፈተና በቂ ልምምድ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ ፈተናው በበይነመረብ መሰጠቱ በቀጣይ ብቁና ተወዳዳሪ ለመሆን ቴክኖሎጂን ይበልጥ እንዲለማመዱ እድል የሚሰጥ መሆኑን አስታውቀዋል ፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ዮርዳኖስ ፍቃዱ እንዳለችው ፈተናው በበይነ መረብ መሰጠቱ ብቁና ተወዳዳሪ ለመሆን የቴክኖሎጂ እውቀትን ለማዳበር ትኩረት እንድንሰጥ ያስችለናል ብላለች። ፈተናውን በራሳችን ዝግጅት ላይ ተመስርቶ በመስራት የጥረታቸንን ዋጋ እንድናገኝ በማድረግ በኩል ትልቅ ጠቀሜታ አለው ያለችው ደግሞ ተማሪ ሜሮን እንዳለ ነች።   ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ተማሪ ናታኒም ኤሊያስ እንዳለችው፤ በዛሬው እለት የወሰዱት የመጨረሻ የልምምድ ፈተና ለዋናው ፈተና ብቁ እንዲሆኑ ሚያስችላቸው መሆኑን ነው የገለጸችው፡፡   ተማሪዎቹ በበይነ መረብ ለሚሰጠው ፈተና በቂ ዝግጅት ለማድረግ በዛሬው እለት የመጨረሻ የልምምድ ፈተና በመፈተን ጥሩ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ተናግራለች።   በልምምድ ወቅት መምህራኖቻቸው የተለያዩ ጥያቄዎችን በማዘጋጀት ለፈተናው እንዲዘጋጁ የሚጠበቅባቸውን ሲያደርጉ እንደነበር የገለጸው ደግሞ ተማሪ ዳግማዊ ታደሰ ነው፡፡ በዛሬው እለት ያደረጉት የመጨረሻ የልምምድ ፈተናም ክፍተቶቻቸውን ለይተው በማስተካከል ለዋናው ሀገር አቀፍ ፈተና እንዲዘጋጁ ያሚያደርጋቸው መሆኑን ተናግሯል፡፡   የመጨረሻው ልምምድ ለዋናው ፈተና ያደረኩትን ዝግጅት ለመፈተሽ ያስቻለኝ ነው ስትል የገለጸችው ደግሞ ተማሪ ዮርዳኖስ አበበ ነች፡፡   ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ ልምምዶችን እና በቂ ዝግጅት በማድረግ ሀገር አቀፍ ፈተናውን በመጠባበቅ ላይ መሆኑን የገለጸው ደግሞ ተማሪ አቤኔዘር ፍቃዱ ነው፡፡        
ዜጎች ደምና የዓይን ብሌን በመለገስ የሚያበረክቱትን በጎ ተግባር አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Jun 14, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ዜጎች ደምና የዓይን ብሌን በመለገስ የሚያበረክቱትን በጎ ተግባር አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ። ዓለም አቀፍ የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ በተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።   የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በመርሀ ግብሩ ላይ እንደገለፁት፤ በኢትዮጵያ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየዳበረ ሲሆን በህብረተሰቡ ዘንድም ደም መለገስ እየተለመደ ነው። ይሁን እንጂ ደም የመለገስ ተግባር ወጥነት እንደሌለው ያነሱት ዶክተር መቅደስ፤ በዘመቻና በንቅናቄ ተግባራት ላይ መመስረቱ ውስንነት እንዲያጋጥመው አድርጎታል ብለዋል። ህብረተሰቡ በራሱ ተነሳሽነት ደም የመለገስ ተግባርን ቀጣይነት ባለው መልኩ እንዲያከናውንም ጥሪ አቅርበዋል። ይህም በደም መፍሰስ ምክንያት የሚከሰት የእናቶች ሞት ለማስቀረት የሚደረገውን ጥረት ከዳር ለማድረስ አይነተኛ ሚና እንዳለው አመልክተዋል። በተለያየ የጤና እክል ምክንያት በቋሚነት ደም ለሚያስፈልጋቸው፣ በተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ አደጋ የደም እጥረት ለሚያጋጥማቸው ሰዎችም የደም አቅርቦት ወሳኝ በመሆኑ ደም የመለገስ ልምዱ እየተጠናከረ መሄድ እንዳለበት ጠቁመዋል። መንግስት የደም ባንኮችን፣ የህክምና ተቋማትንና መሰል ግብዓቶችን በማሟላት ረገድ እያከናወነ ባለው ተግባር አበረታች ውጤት መመዝገቡንም ገልጸዋል። የጤና አገልግሎትን ወጥና ተደራሽ ለማድረግ ዜጎች ደምና የዓይን ብሌን በመለገስ የሚያበረክቱትን አስተዋፅኦ አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ነው ዶክተር መቅደስ የገለጹት።   የኢትዮጵያ ደምና ሕብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አሸናፊ ታዘበው በበኩላቸው፤ አንድ ሰው ደምና የዓይን ብሌን በሚለግስበት ወቅት ተስፋን፣ የወደፊት ብርሀንና ህይወትን መስጠት መሆኑን አስታውቀዋል። ይህም ከስጦታዎች ሁሉ የላቀ ስጦታ መሆኑን ነው የገለጹት። በመረሀ ግብሩ ላይ በተከታታይ ደም የለገሱ ሰዎች እውቅና የተ ሰጣቸው ሲሆን፤ ሰዎች ከህልፈት በኋላ የዓይን ብሌንን እንዲለግሱ ጥሪ የሚቀርብበት ነውም ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰኔ ወር እየተከበረ ያለው 21ኛው የደምና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን "የሕይወትና የብርሀን ስጦታ! ደም ይለግሱ፤ ብሌንዎን ቃል ይግቡ" በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተከበረ ያለው።  
የሚታይ
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደህንነትን በማረጋገጥ ለግንባታው አስተዋጽኦ እያደረግን ነው - የመከላከያ ሠራዊት አመራሮችና አባላት
Jun 14, 2025 73
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ደህንነትን በማረጋገጥ ለግንባታው በተለያየ መልኩ አስተዋጽኦ እያደረገን ነው ሲሉ የመከላከያ ሠራዊት አመራሮችና አባላት ገለጹ። የመላው ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት ታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ደረጃ ላይ መድረሱ እንዳስደሰታቸውም ተናግረዋል። በምዕራብ ዕዝ የ404 ሕዳሴ ኮር ሶስተኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን "ሕዳሴን በሕዳሴ ኮር" በሚል መሪ ሐሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች በማክበር ላይ ይገኛል። የሠራዊቱ አባላትም በዛሬው ዕለት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም የመላው ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ደረጃ ደርሶ በመመልከታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።   የምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ሙላቱ ጀልዴ በጉብኝቱ ወቅት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ደረጃ ለመድረሱ መላው ኢትዮጵያውያን ያላሰለሰ ጥረት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። መከላከያ ሠራዊቱ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እውን እንዲሆን የግድቡን ደህንነት ከማስጠበቅ ጀምሮ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸዋል።   በምዕራብ ዕዝ የሪጅን ሶስት ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ዘመኮንን አበራ እንደገለጹት፤ ሠራዊቱ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ግዳጁን በብቃት ለመወጣት ከምን ጊዜውም በላይ ዝግጁ ነው። ሕዳሴ ኮር የግድቡን አካባቢ ሰላምና ጸጥታ ለማስከበር እያደረገ ያለውን ተግባር በውጤታማነት እየተወጣ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህንን ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   በምዕራብ ዕዝ የ403 ኮር አባል ሌተናል ኮሎኔል ፍሰሃ ጥላሁን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የታላቁ የህዳሴ ግድብ የመላው ኢትዮጵያውያን እስትንፋስ በመሆኑ ሠራዊቱ ሁሌም የአካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ታላቁ የሕደሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ ሠራዊቱ አስፈላጊውን ሁሉ ማበርከቱን ጠቁመዋል። ዛሬ ለደረሰበት የመጠናቀቅ ደረጃ ደርሶ በመመልከታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።   በምዕራብ ዕዝ የ403 ኮር አባል ሌተናል ኮሎኔል ቴዎድሮስ ዘመነ እንዳሉትም፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የይቻላል መንፈስ ማሳያ ነው። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ለሀገር በረከት የመሆን ደረጃ ላይ በመድረሱ መደሰታቸውን ጨምረው ተናግረዋል።
መገናኛ ብዙሃን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በመታገዝ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር መስራት ይገባቸዋል
Jun 14, 2025 98
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በመታገዝ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር መስራት እንዳለባቸው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ገለጹ። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና እሁድ ኤ.አይ ስቱዲዮ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አሰራር ጥበብ ያሰለጠኗቸውን 25 የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች አስመርቀዋል።   ሰልጣኞቹ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የተውጣጡ ናቸው። የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎቹ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ በመታገዝ በይዘት ስራዎች ላይ እሴት መጨመር የሚያስችል የጽንሰ ሃሳብና የተግባር ተኮር ስልጠና የወሰዱ ናቸው። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በምርቃት መርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ ስልጠናው በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚወስድ ነው። በመሆኑም ሰልጣኞች የተማሩትን ወደ ተግባር በመለወጥ ሀገርን ለመቀየር የመስራት ሃላፊነት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር፣ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር፣ የወል ትርክትን ለመፍጠርና ሀገርን ለማበልጸግ የተያዙ ዋና ዋና እቅዶችን ለማሳካት ቴክኖሊጂውን ጥቅም ላይ በመዋል መስራት ይገባል ብለዋል። በተመሳሳይ በተማሩበት ሙያ ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ፊልሞችን በማምረት፣ ሌሎች ሙያተኞችን በማሰልጠን፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ጽንሰ ሃሳብን ግንዛቤ በመፍጠር መስራት እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል። የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የደረሰበትን ደረጃ በመረዳትና በመገናኛ ብዙሃን የይዘት ስራዎች ውስጥ በመጠቀም ለህብረ ብሔራዊ አንድነት ማጠናከርና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር ማዋል እንደሚገባ በአጽኖኦት አንስተዋል። የመገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችም ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ እውቀት እንዲስፋፋ መስራት እንዳለባቸው በማስገንዘብ ተቋማትን በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች የማዘመን ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።   የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ በበኩላቸው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአግባቡ መጠቀም በድህረ እውነት በሀገር ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከል ይረዳል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት እየተሰራ ለሚገኘው የአሰባሳቢ ትርክት ግንባታም አጋዥ መሆኑን ጠቅሰው፤ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የፈጠራ ስራዎችን ለመደገፍ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።   የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ኢ/ር ዶ/ር) በበኩላቸው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እንደ ሀገር ትልቅ ለውጥ ማምጣት ይቻላል ብለዋል። ኢትዮጵያ ዓለም ከደረሰበት የቴክኖሎጂ ደረጃ ጋር ለመሄድ በርካታ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን ጠቁመው፤ መገናኛ ብዙሃንም ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።   በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የወሰዱት ስልጠና ለይዘትና ሌሎች ስራዎች ትልቅ አቅም በመፍጠር የሀገርን ጥቅም ለማስጠበቅ ፋይዳው ትልቅ መሆኑንም የመገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎች ተናግረዋል።   በመሆኑም በተቋሞቻቸው በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የታገዙ ስራዎችን ለመስራት ምቹ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥሩ አረጋግጠዋል። ሰልጣኞቹ በበኩላቸው በስልጠናው ያገኙትን እውቀት የሀገራቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ እንደሚያውሉ ገልጸዋል።
ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ከዓለም ፈጣን የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር የሚያወዳድር ነው
Jun 14, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ በሳይንስ ሙዚየም የተከፈተው ቋሚ ኤግዚቢሽን ኢትዮጵያን ከዓለም ፈጣን የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር የሚያወዳድርና የትውልዱን መጻዒ ዕድል በፈጠራና ምርምር የሚያግዝ መሆኑን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽንን በይፋ ከፍተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገን መስራት፣ ማየት እና መለማመድ የሚፈልጉ ሰዎች በሙሉ የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽንን እየመጡ መመልከት አለባቸው ብለዋል። ኢትዮጵያውያን ነገን መስራት ነገን መለወጥ ከፈለጉ ልጆቻቸውን ወደ ኤግዚቢሽኑ ሊያመጧቸው እንደሚገባም አመልክተዋል። ልጆቻችንም ይህ ትልቅ ዕድል እንደሆነ ተገንዝበው ክረምቱን ይህንን ቋሚ ኤግዚቢሽን በማየት ብዙ ትምህርት መቅሰም አለባቸው ሲሉም ገልጸዋል። ኤግዚቢሽኑ በውስጡ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የአካባቢ፣ የግብርና፣ የውሃና ኢነርጂ፣ የስፔስና አቪየሽን ማሳያ ክፍሎችን አካቷል። በዕለቱ ቋሚ ኤግዚቢሽኑን የቱሪዝም፣ የኪነ ጥበብ፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና ታዋቂ ግለሰቦች ጎብኝተውታል። አስተያየታቸውን የሰጡ ጎብኚዎችም ኢትዮጵያ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ባከናወነቻቸው ሥራዎች መደመማቸውን ነው ያነሱት። የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ነጋ ወዳጆ ቴክኖሎጂን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ምን ያህል ውጤታማ ሊያደርግ እንደሚችል ያየንበት ነው ብለዋል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርትና በሌሎች ዘርፎች አጋዥ በመሆኑ ትውልዱ ሳይንስን በአግባቡ በመረዳት ለአዳዲስ ፈጠራዎች እንዲተጋ የሚያግዝ መሆኑንም አመልክተዋል።   የፍሎውረስ ኢቨንትስ ስራ አስኪያጅ ዮአዳን ጥላሁን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የቋሚ ኤግዚቢሽኑ መከፈት ተማሪዎች ሳይንስ ላይ የተመሰረተ ተጨባጭ ፊልምና ትርኢት የማየት ዕድል እንዲያገኙና ከቴክኖሎጂ ጋር በደንብ እንዲተዋወቁ ያስችላል። በቋሚ ኤግዚቢሽኑ ኢትዮጵያን በዓለም ተወዳዳሪ የሚያደርጉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን አይቻለሁ የሚሉት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ረዳት መምህር ማስተር ምህረት ከድር ናቸው።   ጋዜጠኛ አስካለ ተስፋዬ በበኩሏ፤ በሳይንስ ሙዚየም በቴክኖሎጂ የታገዘ የፈጠራ ትርኢትና ፊልም በአድናቆት መመልከቷን ገልጻለች። ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ትልቋ ኢትዮጵያን ከማሳየት ባለፈ የተፈጥሮ ጸጋ፣ የእድገትና የቴክኖሎጂ ልህቀት መሻቷን የሚያሳይ እንዲሁም ለተማሪዎች የነገ ተስፋ ለተመራማሪዎች ደግሞ ምቹና ሁሉን ያቀፈ ማዕከል መሆኑን ነው ያብራራችው።   ጋዜጠኛ ዮናስ ከበደ በሙዚየሙ የትናንት፣ የዛሬና የነገ ማንነታችንን ያየንበት ነው ብሏል። ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት ከፍታ ትናንትን ያልረሳና ትውልድን ያስተሳሰረ መሆኑ ሁሉንም የሚያኮራ መሆኑን በማንሳት።   ጋዜጠኛ ዳዊት አበበም የሰው ሰራሽ አስተውሎት የሰው ልጆችን ህይወት በማቅለል በኩል የደረሰበትን ደረጃ በቀላሉ ማየትና በዚያ መጠቀም የሚያስችሉ ዕድሎች መፈጠራቸውን አድንቋል።   የሳይንስ ሙዚየምን በሰለጠኑ ሀገራት የመመልከት ዕድል እንደነበረውና በአጭር ጊዜ በኢትዮጵያ እውን ሆኖ ማየቱ አግራሞት እንደፈጠረበት የገለጸው ደግሞ አርቲስት ዳንኤል ተገኝ ነው። በሙዚየሙ ያገኘውን ዕድል ተጠቅሞ ለሀገርና ህዝብ ጠቃሚ የሆነ ፊልም ለመስራት ፍላጎት አንዳደረበት ጠቅሷል።   በቋሚ ኤግዚቢሽኑ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የህዋ ቅርጽ ሉላዊ የትዕይንት አዳራሽ ይፋ የተደረገ ሲሆን ስለ-ህዋ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው እጅግ አስደማሚ ምስሎችን በማቅረብ የህዋውን አለም እጅግ አቅርቦ ያሳያል።
የበረሃ አንበጣና ፀረ ተባይ መከላከያ ቴክኖሎጂን በስፋት በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ ነው - ኮርፖሬሽኑ
Jun 14, 2025 54
አዳማ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የበረሃ አንበጣና ፀረ ተባይ መከላከያ ቴክኖሎጂን በስፋት በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ገለፀ። ኮርፖሬሽኑ ከናሽናል ኤርዌይስና ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በመሆን በቀጣይ የርጭት አውሮፕላን አገልግሎት ተደራሽነትን ማስፋትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችለውን ውይይት በአዳማ ከተማ አካሂዷል።   የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ፈለቀ ገዛኸኝ በወቅቱ እንደገለፁት የበረሃ አንበጣን ከመከላከል ባለፈ የሰብል ምርትና ምርታማነትን የሚቀንሱ ተባዮች ለማጥፋት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ ነው። ኮርፖሬሽኑ የራሱ በሆነ 10ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በ22 የሰብል ዓይነቶች ምርጥ ዘር እያባዛ መሆኑን ተናግረዋል። ኮርፖሬሽኑ አሁን ላይ ተጨማሪ 5ሺህ ሄክታር መሬት ወደ እርሻ በማስገባት የተለያዩ የሰብል ምርጥ ዘሮችን በጥራትና በብዛት ለማምረት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ከናሽናል ኤርዌይስ ጋር በመተባበር በ6ሺህ ሄክታር ላይ የለሙ የተለያዩ የምርጥ ዘር ሰብሎች በአረም፤ በተባይና በሌሎች ተያያዥ የሰብል በሽታዎች እንዳይጎዱ በአውሮፕላን ርጭት መካሄዱን ለአብነት ጠቅሰዋል።   የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ምክትል ስራ አስኪያጅ ጫላ አበበ በበኩላቸው ኢንተርፕራይዙ ከ32ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ60 በላይ የሰብል ዝርያዎችን በማልማት የምርጥ ዘር ፍላጎትን ለማሟላት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንተርፕራይዙ በ2016/17 ምርት ዘመን ከ800ሺህ ኩንታል በላይ የተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ምርጥ ዘር ማምረቱን ጠቅሰው የፀረ አረምና ፀረ ሰብል በሽታ ማጥፊያ የርጭት አውሮፕላን በመጠቀሙና የሰብል እንክብካቤ ስራ በመስራቱ ከ160ሺህ ኩንታል በላይ ተጨማሪ ምርት ማግኘት መቻሉን አስታውቀዋል። ድርጅቱ በዋናነት በምስራቅ ባሌና ባሌ፣ በአርሲና ምዕራብ አርሲ ዞኖች የስንዴ ልማት እንዲሁም በወለጋ በበቆሎ ምርጥ ዘር ላይ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ኢንተርፕራይዙ በተለይ ከናሽናል ኤርዌይስ ጋር በመተባበር የምርጥ ዘር ብዜት ውጤታማነትን አሁን ካለበት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። በ2017/18 የምርት ዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለንን ቅንጅት በማጠናከር ምርታማነትን በተሻለ ደረጃ ለማሳደግ አቅደን እየሰራን ነው ሲሉም አክለዋል።   የናሽናል ኤርዌይስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ካፒቴን አበራ ለሚ በበኩላቸው ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የበረሃ አንበጣን ጨምሮ የአውሮፕላን ፀረ ተባይና ፀረ መድኃኒቶች ርጭት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የግብርና ዘርፍ ዕድገት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የማቅረብ ስራ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በቀጣይም በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ከኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ጋር ተፈራርመዋል።
ለከተማዋ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ባለሙያዎች እያፈራን ነው- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 14, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ለሰው ሃይል ልማት ቅድሚያ ሰጥተን በመስራታችን ለአዲስ አበባ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ባለሙያዎች እያፈራን እንገኛለን ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ “ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን 15ኛውን ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ አውደ ርዕይ መርቀው ከፍተዋል።   አውደ ርዕዩ ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ቀን ክፍት ሆኖ አንደሚቆይ ተገልጿል፡፡ ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ኢትዮጵያ በርካታ የልማት ተግባራትን በማከናወን የብልጽግና መሰረት እየጣለች ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ የምትበለጽገው የራሳችንን የሰው ሀይልና የተፈጥሮ ሀብት አቀናጅተን በማልማት ነው በሚል ጽኑ አቋም በሰራናቸው ስራዎች የብልጽግና መሰረት እየተጣለ ይገኛል ብለዋል። በዚህም አዲስ አበባን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ የከተማ አስተዳደሩ ቀን ከሌት በትኩረት እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት፡፡ እየተከናወኑ ባሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ከፍተኛ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ በሰው ሃይል ልማት ላይ በተሰራው ስራ በከተማዋ ልማት አሻራቸውን ያሳረፉ ባለሙያዎችን ማፍራት መቻሉን አንስተዋል፡፡   የቴክኒክና ሙያ ዕውቀትን የቀሰሙ ባለሙያዎች ለከተማዋ ልማት ትልቅ እገዛ የሚያደርጉ የተለያዩ ችግር ፈቺ ማሽኖችን እያመረቱ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ለኮሪደር ልማቱ ብቁ የሰው ሃይል በማቅረብና የተለያዩ ማሽኖችን በማምረት ያበረከቱትን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለአብነት አንስተዋል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ጥራት ያለው ተኪ ምርት በማምረት ከውጭ የሚገባ ምርትን በማስቀረት ረገድ የራሳቸውን ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከንቲባዋ በዘርፉ የሚነሱ ጥያቄዎችን በመፍታት እና የሚደረገውን ድጋፍ በማጠናከር የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ሚና የበለጠ እንዲጠናከር ይደርጋል ብለዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው ከተማ አስተዳደሩ ባለፉት ሰባት አመታት ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ ተቋማቱን በወርክሾፕ፣ በመሰረተ ልማት፣ በማሽነሪ እና በሰው ሃይል የማጠናከር ስራ ማከናወኑን አስታውቀዋል። በተሰራው ውጤታማ ስራ ኮሌጆቹ ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ሙያ የሚቀስሙባቸው ተቋማት ለመሆን መብቃታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ አውደ ርዕዩ ህብረተሰቡ በዘርፉ የተፈጠረውን አቅም እንዲገነዘብ ለማድረግ የተዘጋጀ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በአውደ ርዕዩ ከ150 በላይ የፈጠራ ውጤቶች ለእይታ የሚቀርቡ ሲሆን የፓናል ውይይቶችና ሌሎች መርኃ ግብሮች እንደሚካሄዱ ተመላክቷል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በክልሉ የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየደረጃው የሚገኙ የምክር ቤት አባላት ሚና ሊጠናከር ይገባል
Jun 14, 2025 52
ጋምቤላ፤ ሰኔ 7/2017 (ኢዜአ)፡-በጋምቤላ ክልል የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና እየተከናወኑ ላሉ ስራዎች ስኬታማነት በየደረጃው የሚገኙ የምክር ቤት አባላት ሚና ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወይዘሮ መሠረት ማቲዎስ አመለከቱ። ከክልል እስከ ወረዳ የሚገኙ ምክር ቤቶች ዓመታዊ የጋራ የምክክር መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሄዷል ።   በምክክር መድረኩ ላይ አፈ ጉባኤዋ እንዳሉት የተዋረድ ምክር ቤቶቹ የወከሉትን ህዝብ በልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተጠቃሚ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች በቋሚ ኮሚቴዎች አማካኝነት አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች የሚያዘጋጇቸው የልማት ዕቅዶች በአግባቡ መተግበራቸውን በመከታተልና በመቆጣጠር የህዝቡን ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ እንደሚገባ አመልክተዋል። በተለይም የመንግስትን ውስን ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ በማዋል ከድህነት ፈጥኖ ለመውጣት ለሚደረገው ጥረት ስኬታማነት ከምክር ቤት አባላት የላቀ ሚና ይጠበቃል ብለዋል። ህዝብ ለሚያነሳቸው የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ከመስጠት አንፃር ምክር ቤቶች ከአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ጋር ያላቸውን ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር እንዳለባቸውም አሳስበዋል። በህገ መንግስቱ የተደነገጉ የዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ሳይሸራረፉ እንዲተገበሩና በውጤቱም ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት መስራት ይጠበቅብናል ሲሉም አፈ-ጉባኤዋ ገልፀዋል። 'የዛሬው የተዋረድ ምክር ቤቶች የጋራ የምክክር መድረክም ልምዶችን በመለዋወጥ የመደጋገፍ ባህላችንን ለማጠናከር ያለመ ነው ብለዋል።   የምክክር መድረኩ አዘጋጅ የጋምቤላ ከተማ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ኩዊች ዊው በበኩላቸው መድረኩ የተዋረድ ምክር ቤቶቹ የውክልና ተግባራቸውን በመፈፀም ረገድ ያሉ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት በቀጣይ ውስንነቶችን ለማረም እገዛ እንዳለውም ተናግረዋል። በዚህም የጋምቤላ ከተማ ምክር ቤት በህገ መንግሥቱ የተሰጠውን ስልጣንና ተግባር በአግባቡ ለመወጣት ከክልሉ ምክር ቤትና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። የተዋረድ ምክር ቤቶች የምክክር መድረክ ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።  
መንግስት ያደሩ ችግሮችን በአምስት ማዕቀፍ ለመፍታት ወስኖ እየሰራ ይገኛል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jun 14, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ያደሩ ችግሮችን በአምስት ማዕቀፍ ለመፍታት በመወሰን እየሰራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ መምህራን ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ከመምህራን ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም የመምህራንን ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተው ነገር ግን ጥያቄው በደሞዝ ጭማሪ ብቻ የሚመለስ አለመሆኑን አብራርተዋል። መንግስት ያደሩ ችግሮችን በአምስት ማዕቀፍ ለመፍታት ወስኖ እየሰራ መሆኑን ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመጀመሪያው አካታች ሀገራዊ ምክክር መሆኑንና ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው እንደሆነ አስታውሰዋል።   እንዲሁም የሽግግር ፍትህ፣ የታጠቁ አካላትን በተሐድሶ መልሶ ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀል(ዲዲአር)፣ የብዝሀ ዘርፍ የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የተቋማት ሪፎርም ሌሎች ማዕቀፎች መሆናቸውን አብራርተዋል። በሌላ በኩል የትምህርት ዘርፋን በጀት በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ፣ የአንድ ዩኒቨርሲቲ በጀት ከትምህርት ሚኒስቴር በጀት እንደሚበልጥና የእያንዳንዱ ዩኒቨርሲቲ በጀት ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። መምህራን ማሰብ ያለባቸው ገበታውን እንዴት እናስፋው የሚለውን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገበታ ለማስፋት ምርታማነት ላይ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። ተቋማትን በማዘመን የመምህራንን ጥያቄ ለመመለስ ይሰራልም ነው ያሉት።   የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ፣ የጋራ ትርክት ግንባታ፣ ምርታማነት፣ የገጠር ኮሪደር እና የትምህርት ጥራት ላይ በጋራ መረባረብ እንደሚያስፈልግ አውስተዋል። ችግሮችን ለመፍታት የተቀመጡ አምስቱ ማዕቀፎችም አድራሽ እንጂ ግብ አይደሉም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለስኬቱ ሁሉም እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል።
መንግስት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በላቀ ቁርጠኝነት እየሰራ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jun 13, 2025 93
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 6/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በላቀ ቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ መምህራን ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በውይይቱ መንግስት በኢትዮጵያ ሰላምን ለማስፈን እያከናወናቸው ያሉ ስራዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። መንግስት የሰላምን ጉዳይ በተቋም እንስራ በሚል የሰላም ሚኒስቴርን ማቋቋሙን አውስተው ከተቋሙ ባሻገር ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ችግሮችን ለመፍታት ያላሰለሰ ጥረት ማድረጉን አመልክተዋል።   ይሁንና መንግስት ለሰላም ያቀረበውን ጥሪ እና የዘረጋውን እጅ ወደ ጎን በመተው ኃይልን እንደ አማራጭ እየተጠቀሙ ያሉ አካላት እንዳሉ ጠቅሰው ከውይይትና ከንግግር ውጪ ሌላ ሰላምን ማምጫ አማራጭ እንደሌለ ሊገነዘቡ ይገባል ብለዋል። ጥሪውን ተቀብለው በሰላማዊ መንገድ እጃቸውን የሰጡ ታጣቂዎችን ከመቀበል ባለፈ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በማድረግ ጭምር መንግስት ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በግልጽ ማሳየቱን አመልክተዋል። ለኢትዮጵያ ሰላም ሲባል ችግሮችን በውይይት መፍታት ለሚፈልግ እና የተሻለ ሀሳብ አለኝ ላለ ማንኛውም አካል መንግስት ሁሌም በሩ ክፍት ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግስት የሰላም ጥሪን ወደ ጎን በመተው ሰውን ማገትና ትምህርት ቤት ማዘጋትን ጨምሮ የኃይል አማራጭን በወሰዱ ኃይሎች ላይ የሕግ ማስከበር እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታውቀዋል።   የፕሪቶሪያ ንግግር መንግስት ለሰላም ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠበት ነው ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ሰላም ያስፈጋታል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይህ እንዲሆን መንግስት በከፍተኛ ትጋት እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ሰላም የሚሹ ኃይሎችን የሰላም ግንባታው ሂደት አካል በማድረግ በጋራ እንሰራለን ሲሉም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን በጎ ገጽታ በዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ መድረኮች ለማስተዋወቅ የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ ይጠይቃል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
Jun 13, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 6/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን በጎ ገጽታ በዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ መድረኮች ለማስተዋወቅ ከመደበኛው የመንግሥት ሥራ በተጨማሪ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ዜጎች በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ገለጹ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የውጭ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር በመተባበር ለወዳጅነት ቡድኖችና ፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ያዘጋጁት ስልጠና ተጀምሯል። ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ፣ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ፣ የጎረቤት ሀገራትና የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ እንዲሁም ሌሎች የውጭ ግንኙነት ስልቶች ይዳሰሳሉ፡፡   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ሀገራዊ ልማትና ብልጽግናን እውን ለማድረግ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ እና የተደራጀ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል። ለዚህ ደግሞ የዓለም ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስርዓቱ የሚጠይቀውን የውጭ ግንኙነት ስልት መንደፍና መከተል አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው፤ የዓለም አስቻይ ሁኔታዎችን በጥንቃቄ በማየት በአስተውሎት መራመድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በዚህም የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ፣ አጋርነትን ለማጠናከር፣ ገጽታ ለመገንባት፣ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ሁሉም አካላት በጋራ መረባረብ አለባቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ ገልጸው፤ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ ስትራቴጂያዊ አጋሮችን የማብዛት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል።   በመርህ ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፋዊ እና ቀጣናዊ አጋርነትን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በባለብዙ ወገን መድረኮች የሚተላለፉ ውሳኔዎች የኢትዮጵያን ተደማጭነትና ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቁ እንዲሆኑ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ የአፍሪካ የነፃነት ተምሳሌት፣ እንዲሁም የብዝሀ ብሔር መገኛ መሆኗን በፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራችን መግለጽና ገጽታዋን መገንባት አለብን ሲሉም አስገንዝበዋል። ለዚህ ደግሞ መንግስት ከሚሰራው የውጭ ግንኙነት ስራዎች ባሻገር በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡   በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሽብሩ ማሞ በበኩላቸው፤ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ የሀገራችን መልካም ገጽታ መገንባት፣ አጋርነትና ወዳጅነትን ማብዛት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ በመንግሥታት ግንኙነት ብቻ የታጠረውን የሀገራት ግንኙነት በህዝቦች መካከል እንዲዳብር ያስቻለ ነው ብለዋል፡፡ በተለይም የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የምርምር ተቋማትና የተለያዩ የሙያ ማህበራት የሀገርን ገጽታ በማስተዋወቅ በኩል ሚናቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
እየተካሔዱ ያሉ የህዝብ ውይይቶች ዜጎች ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የበኩላቸውን እንዲወጡ የሚያግዙ ናቸው
Jun 13, 2025 82
ሚዛን አማን፤ ሰኔ 6/2017(ኢዜአ)፦እየተካሔዱ ያሉ የሕዝብ ውይይቶች ዜጎች ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በአግባቡ በመረዳት ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የበኩላቸውን እንዲወጡ እንደሚያግዙ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። መንግስት በዞን፣ በክልልና በከተሞች ደረጃ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ተከታታይ ውይይት እያደረገ ይገኛል። ሰሞኑንም ይኽው ውይይት ቀጥሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ከተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች ከተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት እያደረጉ ነው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንም መንግስት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከዜጎች ጋር እያደረገ ያለው ውይይት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መጠናከር ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ጥናት ትምህርት ክፍል መምህር ዋሲሁን በዛብህ እንዳሉት ዜጎች ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በአግባቡ በመረዳት ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የበኩላቸውን እንዲወጡ ተከታታይ ውይይቶች አስፈላጊ ናቸው። ከዚህም ባለፈ እየተደረጉ ያሉ ተከታታይ ውይይቶች የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለዜጎች ለማስገንዘብና አገራዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የጋራ ርብርብ እንዲደረግ ያግዛል ብለዋል። የሀገር ግንባታ የሁሉንም የነቃ ተሳትፎ ይጠይቃል ያሉት መምህር ዋሲሁን ለተግባራዊነቱም መሰል ውይይቶች በሀገራዊ ጉዳይ የጋራ አረዳድ በመያዝ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲዳብር እንደሚያግዝ አመልክተዋል። በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በሪሁን በበኩላቸው እየተካሄዱ ያሉ ውይይቶች ልማትን ለማፋጠንና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር ያግዛሉ ብለዋል። መንግሥትም ከዜጎች የሚነሱ ጥያቄዎችን በቅርበት ተረድቶ እንደ አስፈላጊነቱ ምላሽ እንዲሰጣቸው ትልቅ እድል ይፈጥራል ሲሉም ገልጸዋል። በተጨማሪም ውይይቶቹ መንግስት ብሔራዊ ጥቅሞችን ለማስከበር የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት ማኅበረሰቡ ነባራዊ ሁኔታዎችን ተገንዝቦ የበኩሉን ድርሻ እንዲያጠናክር የሚያደርግ እንደሆነም አመልክተዋል። በመንግሥትና ሕዝብ መካከል ግልጸኝነትን ለመፍጠር የሚደረጉ መሰል የውይይቶች ለዴሞክራሲ ግንባታ ትልቅ ትርጉም አላቸው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር አለማየሁ አብርሃም ናቸው። በተለይም መንግስት ከምሁራን ጋር የሚያደርገውን ውይይት በማጠናከር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን የሚያገኝበት መሆኑንም ተናግረዋል።  
ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ማጠናከር ይገባል- አምባሳደር ሃደራ አበራ
Jun 13, 2025 107
አዲስ አበባ፤ሰኔ 6/2017 (ኢዜአ)፦ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ እና የተደራጁ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር በመተባበር ለወዳጅነት ቡድኖችና ፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ያዘጋጀው ስልጠና ተጀምሯል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ሀገራዊ ልማትና ብልጽግናን እውን ለማድረግ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ፣ አጋርነትን ለማጠናከር፣ገጽታ ለመገንባት፣ የዜጎችን ጥቅም ለማስከበር እና የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ሁሉም አካላት በጋራ መረባረብ አለባቸው ብለዋል። ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ እና የተደራጀ የዲፕሎማሲ ስራ ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል። ለዚህ ደግሞ የዓለም ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስርዓቱ የሚጠይቀውን የውጭ ግንኙነት ስልት መንደፍና መከተል፤የዓለም አስቻይ ሁኔታዎችን በጥንቃቄ በማየት በአስተውሎት መራመድ እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን ገልጸው፤የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ ስትራቴጂያዊ አጋሮች የማብዛት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ብሔራዊ ጥቅሟን ማስጠበቅ የሚያስችሉ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸው፣ በመርህ ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፋዊ እና ቀጣናዊ አጋርነትን ማሳድግ ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል። ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣የአፍሪካ የነፃነት ተምሳሌት፣ እንዲሁም የብዝሀ ብሔር መገኛ መሆኗን በፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራችን መግለጽና ገጽታዋን መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል። ለዚህ ደግሞ መንግስት ከሚሰራው የውጭ ግንኙነት ስራ ባሻገር በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ፊንላንድ በተለያየ መስክ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት ታጠናክራለች - የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሊና ቫልቶነን
Jun 12, 2025 160
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦ፊንላንድ በተለያየ መስክ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት እንደምታጠናክር የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሊና ቫልቶነን ተናገሩ። ፊንላንድ ለስምንት ተከታታይ ዓመታት በዓለም ቁጥር አንድ የደስተኞች አገር በመባል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተሰይማለች። ይህን መነሻ በማድረግ በሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋባዥነት የአፍሪካ ጋዜጠኞች በቅርቡ በፊንላንድ ጉብኝት አካሂደዋል። በዚህ ወቅት የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሊና ቫልቶነን ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ፊንላንድና ኢትዮጵያ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው። ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዘርፈ-ብዙ ግንኙነት ማጠናከር እንደምትፈልግ የገለጹት ሚኒስትሯ በተለይም በልማት፣ በንግድና ኢንቨስትመንት መስኮች የበለጠ ትኩረት እንደሚደረግ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያና የፊንላንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከተመሰረተ 66 ዓመታትን አስቆጥሯል። ሁለቱ ሀገራት ለረጅም ዓመታት የቆየ በጋራ ጥቅምና መተማመን ላይ የተመሰረተ የሁለትዮሽ ግንኙነትም አላቸው። የልማት ትብብራቸው በትምህርት፣ በገጠር ልማት፤ በንግድና ኢንቨስትመንት እና በሌሎችም መስኮች ላይ ያተኮረ ነው። ይህ ዘርፈ-ብዙ የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ያድጋል የሚል እምነት እንዳላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ኤሊና ቫልቶነን ተናግረዋል።   በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽንስ ጉዳዮች አምባሳደር አን ላሚላ በበኩላቸው ለኢዜአ እንደገለጹት የሚዲያ ጉብኝቱ ዓላማ ስለ ፊንላንድ ማሳወቅና የስኬት ምስጢሮችን ማካፈል ብቻ ሳይሆን ሀገሪቱ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ማሳደግ ጭምር ነው። ፊንላንድ ከአፍሪካ ሕብረት፤ በተናጥልም ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጋር ስትራቴጂክ አጋርነት እንዳላት የገለጹት አምባሳደሯ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ግንኙነትም ጠንካራ መሰረት ያለው መሆኑን አስታውሰዋል። የደስተኛ ህዝቦች መኖሪያ የምትሰኘው ፊንላንድ ግብር ከፋይ የአገሪቱ ዜጎች በታማኝነትና በደስታ ግብር የሚከፍሉባት ሰሜን አውሮፓዊት ሀገር ነች። በትምህርት፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በጾታ እኩልነት፤ እንዲሁም በጤናና ለማህበረሰብ ምቹ ቤተሰብ መፍጠርን ጨምሮ ባከናወነቻቸው ጠንካራ የማህበራዊ ደህንነት ትስስር ስራዎች ዜጎቿ ደስተኞች መሆናቸው ይገለጻል።
አርሜኒያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ ወዳጅነት ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትሰራለች - ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታንያን
Jun 12, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦ አርሜኒያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ ወዳጅነት ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደምትሰራ የአርሜኒያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታንያን ገለጹ። የአርሜኒያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታንያን እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያና አርሜኒያ ታሪካዊና ጠንካራ የሁለትዮሽ ወዳጅነት አላቸው። በአራተኛው ክፍለ ዘመን የተጀመረው የኢትዮጵያና አርሜኒያ ግንኙነት እያደገና ዘላቂ ወዳጅነት እያስመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በአዲስ አበባ የሚታየው የአርሜኒያ ህዝቦች አሻራም የሁለቱን ሀገራት የህዝብ ለህዝብ ጥልቅ ወዳጅነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚገኙት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የአርሜኒያ ማህበረሰብም በአዲስ አበባ በንግድና በዕደ-ጥበብ ሙያ በመሰማራት ከኢትዮጵያዊያን ጋር በጥብቅ ወዳጅነትና አብሮነት እየኖሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአዲስ አበባ የአርሜኒያዊያን የስራ ባህል ውርስ የሆኑ ጌጣ ጌጦች፣ ኪነ-ጥበበኞች፣ ነጋዴዎችና የተለያዩ የሙያ ጠበብቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅትም በኢትዮጵያና አርሜኒያ መካከል አንዳቸው ለአንዳቸው ቅርብ አጋር የሚሆኑበት ከፍተኛ ዕድል መኖሩን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አክለዋል። የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውም የኢትዮ-አርሜንያን ህዝቦች የባህል፣ የትምህርት፣ ቴክኖሎጂና የጤና መስክ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አብራርተዋል። ለአብነትም በኢትዮ-አርሜኒያን መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር የሳይንስ፣ የባህልና ትምህርት ስምምነት መፈረሙን አስታውሰዋል። በቀጣይም የጋራ የመንግስታት ኮሚሽን በማቋቋም የፖለቲካና ሌሎች የትብብር መስኮችን ለማጠናከር የሃሳብ ልውውጥ መደረጉን አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ቆይታቸውም ፖለቲካዊ ምክክር፣ ቀጣናዊ፣ አፍሪካዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮችን የዳሰሰ መሆኑን አስረድተዋል። በምክክር መድረኩም ኢትዮጵያና አርሜኒያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅትና በሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት አባልነታቸውን በመጠቀም ያላቸውን የነቃ ተሳትፎ ለማጠናከር አጽንኦት እንደተሰጠ አብራርተዋል።  
ፖለቲካ
በክልሉ የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየደረጃው የሚገኙ የምክር ቤት አባላት ሚና ሊጠናከር ይገባል
Jun 14, 2025 52
ጋምቤላ፤ ሰኔ 7/2017 (ኢዜአ)፡-በጋምቤላ ክልል የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና እየተከናወኑ ላሉ ስራዎች ስኬታማነት በየደረጃው የሚገኙ የምክር ቤት አባላት ሚና ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወይዘሮ መሠረት ማቲዎስ አመለከቱ። ከክልል እስከ ወረዳ የሚገኙ ምክር ቤቶች ዓመታዊ የጋራ የምክክር መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሄዷል ።   በምክክር መድረኩ ላይ አፈ ጉባኤዋ እንዳሉት የተዋረድ ምክር ቤቶቹ የወከሉትን ህዝብ በልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተጠቃሚ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች በቋሚ ኮሚቴዎች አማካኝነት አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች የሚያዘጋጇቸው የልማት ዕቅዶች በአግባቡ መተግበራቸውን በመከታተልና በመቆጣጠር የህዝቡን ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ እንደሚገባ አመልክተዋል። በተለይም የመንግስትን ውስን ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ በማዋል ከድህነት ፈጥኖ ለመውጣት ለሚደረገው ጥረት ስኬታማነት ከምክር ቤት አባላት የላቀ ሚና ይጠበቃል ብለዋል። ህዝብ ለሚያነሳቸው የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ከመስጠት አንፃር ምክር ቤቶች ከአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ጋር ያላቸውን ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር እንዳለባቸውም አሳስበዋል። በህገ መንግስቱ የተደነገጉ የዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ሳይሸራረፉ እንዲተገበሩና በውጤቱም ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት መስራት ይጠበቅብናል ሲሉም አፈ-ጉባኤዋ ገልፀዋል። 'የዛሬው የተዋረድ ምክር ቤቶች የጋራ የምክክር መድረክም ልምዶችን በመለዋወጥ የመደጋገፍ ባህላችንን ለማጠናከር ያለመ ነው ብለዋል።   የምክክር መድረኩ አዘጋጅ የጋምቤላ ከተማ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ኩዊች ዊው በበኩላቸው መድረኩ የተዋረድ ምክር ቤቶቹ የውክልና ተግባራቸውን በመፈፀም ረገድ ያሉ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት በቀጣይ ውስንነቶችን ለማረም እገዛ እንዳለውም ተናግረዋል። በዚህም የጋምቤላ ከተማ ምክር ቤት በህገ መንግሥቱ የተሰጠውን ስልጣንና ተግባር በአግባቡ ለመወጣት ከክልሉ ምክር ቤትና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። የተዋረድ ምክር ቤቶች የምክክር መድረክ ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።  
መንግስት ያደሩ ችግሮችን በአምስት ማዕቀፍ ለመፍታት ወስኖ እየሰራ ይገኛል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jun 14, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ያደሩ ችግሮችን በአምስት ማዕቀፍ ለመፍታት በመወሰን እየሰራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ መምህራን ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ከመምህራን ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም የመምህራንን ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተው ነገር ግን ጥያቄው በደሞዝ ጭማሪ ብቻ የሚመለስ አለመሆኑን አብራርተዋል። መንግስት ያደሩ ችግሮችን በአምስት ማዕቀፍ ለመፍታት ወስኖ እየሰራ መሆኑን ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመጀመሪያው አካታች ሀገራዊ ምክክር መሆኑንና ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው እንደሆነ አስታውሰዋል።   እንዲሁም የሽግግር ፍትህ፣ የታጠቁ አካላትን በተሐድሶ መልሶ ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀል(ዲዲአር)፣ የብዝሀ ዘርፍ የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የተቋማት ሪፎርም ሌሎች ማዕቀፎች መሆናቸውን አብራርተዋል። በሌላ በኩል የትምህርት ዘርፋን በጀት በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ፣ የአንድ ዩኒቨርሲቲ በጀት ከትምህርት ሚኒስቴር በጀት እንደሚበልጥና የእያንዳንዱ ዩኒቨርሲቲ በጀት ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። መምህራን ማሰብ ያለባቸው ገበታውን እንዴት እናስፋው የሚለውን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገበታ ለማስፋት ምርታማነት ላይ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። ተቋማትን በማዘመን የመምህራንን ጥያቄ ለመመለስ ይሰራልም ነው ያሉት።   የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ፣ የጋራ ትርክት ግንባታ፣ ምርታማነት፣ የገጠር ኮሪደር እና የትምህርት ጥራት ላይ በጋራ መረባረብ እንደሚያስፈልግ አውስተዋል። ችግሮችን ለመፍታት የተቀመጡ አምስቱ ማዕቀፎችም አድራሽ እንጂ ግብ አይደሉም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለስኬቱ ሁሉም እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል።
መንግስት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በላቀ ቁርጠኝነት እየሰራ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jun 13, 2025 93
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 6/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በላቀ ቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ መምህራን ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በውይይቱ መንግስት በኢትዮጵያ ሰላምን ለማስፈን እያከናወናቸው ያሉ ስራዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። መንግስት የሰላምን ጉዳይ በተቋም እንስራ በሚል የሰላም ሚኒስቴርን ማቋቋሙን አውስተው ከተቋሙ ባሻገር ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ችግሮችን ለመፍታት ያላሰለሰ ጥረት ማድረጉን አመልክተዋል።   ይሁንና መንግስት ለሰላም ያቀረበውን ጥሪ እና የዘረጋውን እጅ ወደ ጎን በመተው ኃይልን እንደ አማራጭ እየተጠቀሙ ያሉ አካላት እንዳሉ ጠቅሰው ከውይይትና ከንግግር ውጪ ሌላ ሰላምን ማምጫ አማራጭ እንደሌለ ሊገነዘቡ ይገባል ብለዋል። ጥሪውን ተቀብለው በሰላማዊ መንገድ እጃቸውን የሰጡ ታጣቂዎችን ከመቀበል ባለፈ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በማድረግ ጭምር መንግስት ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በግልጽ ማሳየቱን አመልክተዋል። ለኢትዮጵያ ሰላም ሲባል ችግሮችን በውይይት መፍታት ለሚፈልግ እና የተሻለ ሀሳብ አለኝ ላለ ማንኛውም አካል መንግስት ሁሌም በሩ ክፍት ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግስት የሰላም ጥሪን ወደ ጎን በመተው ሰውን ማገትና ትምህርት ቤት ማዘጋትን ጨምሮ የኃይል አማራጭን በወሰዱ ኃይሎች ላይ የሕግ ማስከበር እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታውቀዋል።   የፕሪቶሪያ ንግግር መንግስት ለሰላም ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠበት ነው ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ሰላም ያስፈጋታል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይህ እንዲሆን መንግስት በከፍተኛ ትጋት እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ሰላም የሚሹ ኃይሎችን የሰላም ግንባታው ሂደት አካል በማድረግ በጋራ እንሰራለን ሲሉም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን በጎ ገጽታ በዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ መድረኮች ለማስተዋወቅ የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ ይጠይቃል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
Jun 13, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 6/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን በጎ ገጽታ በዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ መድረኮች ለማስተዋወቅ ከመደበኛው የመንግሥት ሥራ በተጨማሪ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ዜጎች በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ገለጹ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የውጭ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር በመተባበር ለወዳጅነት ቡድኖችና ፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ያዘጋጁት ስልጠና ተጀምሯል። ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ፣ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ፣ የጎረቤት ሀገራትና የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ እንዲሁም ሌሎች የውጭ ግንኙነት ስልቶች ይዳሰሳሉ፡፡   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ሀገራዊ ልማትና ብልጽግናን እውን ለማድረግ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ እና የተደራጀ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል። ለዚህ ደግሞ የዓለም ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስርዓቱ የሚጠይቀውን የውጭ ግንኙነት ስልት መንደፍና መከተል አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው፤ የዓለም አስቻይ ሁኔታዎችን በጥንቃቄ በማየት በአስተውሎት መራመድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በዚህም የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ፣ አጋርነትን ለማጠናከር፣ ገጽታ ለመገንባት፣ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ሁሉም አካላት በጋራ መረባረብ አለባቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ ገልጸው፤ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ ስትራቴጂያዊ አጋሮችን የማብዛት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል።   በመርህ ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፋዊ እና ቀጣናዊ አጋርነትን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በባለብዙ ወገን መድረኮች የሚተላለፉ ውሳኔዎች የኢትዮጵያን ተደማጭነትና ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቁ እንዲሆኑ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ የአፍሪካ የነፃነት ተምሳሌት፣ እንዲሁም የብዝሀ ብሔር መገኛ መሆኗን በፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራችን መግለጽና ገጽታዋን መገንባት አለብን ሲሉም አስገንዝበዋል። ለዚህ ደግሞ መንግስት ከሚሰራው የውጭ ግንኙነት ስራዎች ባሻገር በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡   በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሽብሩ ማሞ በበኩላቸው፤ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ የሀገራችን መልካም ገጽታ መገንባት፣ አጋርነትና ወዳጅነትን ማብዛት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ በመንግሥታት ግንኙነት ብቻ የታጠረውን የሀገራት ግንኙነት በህዝቦች መካከል እንዲዳብር ያስቻለ ነው ብለዋል፡፡ በተለይም የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የምርምር ተቋማትና የተለያዩ የሙያ ማህበራት የሀገርን ገጽታ በማስተዋወቅ በኩል ሚናቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
እየተካሔዱ ያሉ የህዝብ ውይይቶች ዜጎች ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የበኩላቸውን እንዲወጡ የሚያግዙ ናቸው
Jun 13, 2025 82
ሚዛን አማን፤ ሰኔ 6/2017(ኢዜአ)፦እየተካሔዱ ያሉ የሕዝብ ውይይቶች ዜጎች ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በአግባቡ በመረዳት ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የበኩላቸውን እንዲወጡ እንደሚያግዙ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። መንግስት በዞን፣ በክልልና በከተሞች ደረጃ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ተከታታይ ውይይት እያደረገ ይገኛል። ሰሞኑንም ይኽው ውይይት ቀጥሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ከተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች ከተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት እያደረጉ ነው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንም መንግስት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከዜጎች ጋር እያደረገ ያለው ውይይት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መጠናከር ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ጥናት ትምህርት ክፍል መምህር ዋሲሁን በዛብህ እንዳሉት ዜጎች ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በአግባቡ በመረዳት ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የበኩላቸውን እንዲወጡ ተከታታይ ውይይቶች አስፈላጊ ናቸው። ከዚህም ባለፈ እየተደረጉ ያሉ ተከታታይ ውይይቶች የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለዜጎች ለማስገንዘብና አገራዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የጋራ ርብርብ እንዲደረግ ያግዛል ብለዋል። የሀገር ግንባታ የሁሉንም የነቃ ተሳትፎ ይጠይቃል ያሉት መምህር ዋሲሁን ለተግባራዊነቱም መሰል ውይይቶች በሀገራዊ ጉዳይ የጋራ አረዳድ በመያዝ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲዳብር እንደሚያግዝ አመልክተዋል። በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በሪሁን በበኩላቸው እየተካሄዱ ያሉ ውይይቶች ልማትን ለማፋጠንና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር ያግዛሉ ብለዋል። መንግሥትም ከዜጎች የሚነሱ ጥያቄዎችን በቅርበት ተረድቶ እንደ አስፈላጊነቱ ምላሽ እንዲሰጣቸው ትልቅ እድል ይፈጥራል ሲሉም ገልጸዋል። በተጨማሪም ውይይቶቹ መንግስት ብሔራዊ ጥቅሞችን ለማስከበር የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት ማኅበረሰቡ ነባራዊ ሁኔታዎችን ተገንዝቦ የበኩሉን ድርሻ እንዲያጠናክር የሚያደርግ እንደሆነም አመልክተዋል። በመንግሥትና ሕዝብ መካከል ግልጸኝነትን ለመፍጠር የሚደረጉ መሰል የውይይቶች ለዴሞክራሲ ግንባታ ትልቅ ትርጉም አላቸው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር አለማየሁ አብርሃም ናቸው። በተለይም መንግስት ከምሁራን ጋር የሚያደርገውን ውይይት በማጠናከር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን የሚያገኝበት መሆኑንም ተናግረዋል።  
ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ማጠናከር ይገባል- አምባሳደር ሃደራ አበራ
Jun 13, 2025 107
አዲስ አበባ፤ሰኔ 6/2017 (ኢዜአ)፦ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ እና የተደራጁ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር በመተባበር ለወዳጅነት ቡድኖችና ፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ያዘጋጀው ስልጠና ተጀምሯል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ሀገራዊ ልማትና ብልጽግናን እውን ለማድረግ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ፣ አጋርነትን ለማጠናከር፣ገጽታ ለመገንባት፣ የዜጎችን ጥቅም ለማስከበር እና የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ሁሉም አካላት በጋራ መረባረብ አለባቸው ብለዋል። ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ እና የተደራጀ የዲፕሎማሲ ስራ ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል። ለዚህ ደግሞ የዓለም ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስርዓቱ የሚጠይቀውን የውጭ ግንኙነት ስልት መንደፍና መከተል፤የዓለም አስቻይ ሁኔታዎችን በጥንቃቄ በማየት በአስተውሎት መራመድ እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን ገልጸው፤የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ ስትራቴጂያዊ አጋሮች የማብዛት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ብሔራዊ ጥቅሟን ማስጠበቅ የሚያስችሉ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸው፣ በመርህ ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፋዊ እና ቀጣናዊ አጋርነትን ማሳድግ ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል። ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣የአፍሪካ የነፃነት ተምሳሌት፣ እንዲሁም የብዝሀ ብሔር መገኛ መሆኗን በፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራችን መግለጽና ገጽታዋን መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል። ለዚህ ደግሞ መንግስት ከሚሰራው የውጭ ግንኙነት ስራ ባሻገር በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ፊንላንድ በተለያየ መስክ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት ታጠናክራለች - የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሊና ቫልቶነን
Jun 12, 2025 160
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦ፊንላንድ በተለያየ መስክ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት እንደምታጠናክር የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሊና ቫልቶነን ተናገሩ። ፊንላንድ ለስምንት ተከታታይ ዓመታት በዓለም ቁጥር አንድ የደስተኞች አገር በመባል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተሰይማለች። ይህን መነሻ በማድረግ በሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋባዥነት የአፍሪካ ጋዜጠኞች በቅርቡ በፊንላንድ ጉብኝት አካሂደዋል። በዚህ ወቅት የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሊና ቫልቶነን ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ፊንላንድና ኢትዮጵያ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው። ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዘርፈ-ብዙ ግንኙነት ማጠናከር እንደምትፈልግ የገለጹት ሚኒስትሯ በተለይም በልማት፣ በንግድና ኢንቨስትመንት መስኮች የበለጠ ትኩረት እንደሚደረግ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያና የፊንላንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከተመሰረተ 66 ዓመታትን አስቆጥሯል። ሁለቱ ሀገራት ለረጅም ዓመታት የቆየ በጋራ ጥቅምና መተማመን ላይ የተመሰረተ የሁለትዮሽ ግንኙነትም አላቸው። የልማት ትብብራቸው በትምህርት፣ በገጠር ልማት፤ በንግድና ኢንቨስትመንት እና በሌሎችም መስኮች ላይ ያተኮረ ነው። ይህ ዘርፈ-ብዙ የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ያድጋል የሚል እምነት እንዳላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ኤሊና ቫልቶነን ተናግረዋል።   በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽንስ ጉዳዮች አምባሳደር አን ላሚላ በበኩላቸው ለኢዜአ እንደገለጹት የሚዲያ ጉብኝቱ ዓላማ ስለ ፊንላንድ ማሳወቅና የስኬት ምስጢሮችን ማካፈል ብቻ ሳይሆን ሀገሪቱ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ማሳደግ ጭምር ነው። ፊንላንድ ከአፍሪካ ሕብረት፤ በተናጥልም ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጋር ስትራቴጂክ አጋርነት እንዳላት የገለጹት አምባሳደሯ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ግንኙነትም ጠንካራ መሰረት ያለው መሆኑን አስታውሰዋል። የደስተኛ ህዝቦች መኖሪያ የምትሰኘው ፊንላንድ ግብር ከፋይ የአገሪቱ ዜጎች በታማኝነትና በደስታ ግብር የሚከፍሉባት ሰሜን አውሮፓዊት ሀገር ነች። በትምህርት፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በጾታ እኩልነት፤ እንዲሁም በጤናና ለማህበረሰብ ምቹ ቤተሰብ መፍጠርን ጨምሮ ባከናወነቻቸው ጠንካራ የማህበራዊ ደህንነት ትስስር ስራዎች ዜጎቿ ደስተኞች መሆናቸው ይገለጻል።
አርሜኒያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ ወዳጅነት ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትሰራለች - ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታንያን
Jun 12, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦ አርሜኒያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ ወዳጅነት ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደምትሰራ የአርሜኒያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታንያን ገለጹ። የአርሜኒያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫሃን ኮስታንያን እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያና አርሜኒያ ታሪካዊና ጠንካራ የሁለትዮሽ ወዳጅነት አላቸው። በአራተኛው ክፍለ ዘመን የተጀመረው የኢትዮጵያና አርሜኒያ ግንኙነት እያደገና ዘላቂ ወዳጅነት እያስመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በአዲስ አበባ የሚታየው የአርሜኒያ ህዝቦች አሻራም የሁለቱን ሀገራት የህዝብ ለህዝብ ጥልቅ ወዳጅነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚገኙት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የአርሜኒያ ማህበረሰብም በአዲስ አበባ በንግድና በዕደ-ጥበብ ሙያ በመሰማራት ከኢትዮጵያዊያን ጋር በጥብቅ ወዳጅነትና አብሮነት እየኖሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአዲስ አበባ የአርሜኒያዊያን የስራ ባህል ውርስ የሆኑ ጌጣ ጌጦች፣ ኪነ-ጥበበኞች፣ ነጋዴዎችና የተለያዩ የሙያ ጠበብቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅትም በኢትዮጵያና አርሜኒያ መካከል አንዳቸው ለአንዳቸው ቅርብ አጋር የሚሆኑበት ከፍተኛ ዕድል መኖሩን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አክለዋል። የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውም የኢትዮ-አርሜንያን ህዝቦች የባህል፣ የትምህርት፣ ቴክኖሎጂና የጤና መስክ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አብራርተዋል። ለአብነትም በኢትዮ-አርሜኒያን መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር የሳይንስ፣ የባህልና ትምህርት ስምምነት መፈረሙን አስታውሰዋል። በቀጣይም የጋራ የመንግስታት ኮሚሽን በማቋቋም የፖለቲካና ሌሎች የትብብር መስኮችን ለማጠናከር የሃሳብ ልውውጥ መደረጉን አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ቆይታቸውም ፖለቲካዊ ምክክር፣ ቀጣናዊ፣ አፍሪካዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮችን የዳሰሰ መሆኑን አስረድተዋል። በምክክር መድረኩም ኢትዮጵያና አርሜኒያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅትና በሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት አባልነታቸውን በመጠቀም ያላቸውን የነቃ ተሳትፎ ለማጠናከር አጽንኦት እንደተሰጠ አብራርተዋል።  
ማህበራዊ
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በበይነ መረብ ለመፈተን የሚያስችል በቂ ልምምድ አድርገናል-በአዲስ አበባ ተፈታኝ ተማሪዎች
Jun 14, 2025 46
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በበይነ መረብ ለመፈተን የሚያስችል በቂ ልምምድና ዝግጅት ማድረጋቸውን በአዲስ አበባ የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪዎች ተናገሩ፡፡ በአዲስ አበባ ለተፈታኝ ተማሪዎች በበይነ መረብ ለሚሰጠው ፈተና የመጨረሻ የልምምድ ፈተና ዛሬ ተሰጥቷል፡፡   የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በዚሁ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ ትምህርት ቤቶች የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች እንደተናገሩት በበይነ መረብ ለሚሰጠው ፈተና በቂ ልምምድ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ ፈተናው በበይነመረብ መሰጠቱ በቀጣይ ብቁና ተወዳዳሪ ለመሆን ቴክኖሎጂን ይበልጥ እንዲለማመዱ እድል የሚሰጥ መሆኑን አስታውቀዋል ፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ዮርዳኖስ ፍቃዱ እንዳለችው ፈተናው በበይነ መረብ መሰጠቱ ብቁና ተወዳዳሪ ለመሆን የቴክኖሎጂ እውቀትን ለማዳበር ትኩረት እንድንሰጥ ያስችለናል ብላለች። ፈተናውን በራሳችን ዝግጅት ላይ ተመስርቶ በመስራት የጥረታቸንን ዋጋ እንድናገኝ በማድረግ በኩል ትልቅ ጠቀሜታ አለው ያለችው ደግሞ ተማሪ ሜሮን እንዳለ ነች።   ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ተማሪ ናታኒም ኤሊያስ እንዳለችው፤ በዛሬው እለት የወሰዱት የመጨረሻ የልምምድ ፈተና ለዋናው ፈተና ብቁ እንዲሆኑ ሚያስችላቸው መሆኑን ነው የገለጸችው፡፡   ተማሪዎቹ በበይነ መረብ ለሚሰጠው ፈተና በቂ ዝግጅት ለማድረግ በዛሬው እለት የመጨረሻ የልምምድ ፈተና በመፈተን ጥሩ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ተናግራለች።   በልምምድ ወቅት መምህራኖቻቸው የተለያዩ ጥያቄዎችን በማዘጋጀት ለፈተናው እንዲዘጋጁ የሚጠበቅባቸውን ሲያደርጉ እንደነበር የገለጸው ደግሞ ተማሪ ዳግማዊ ታደሰ ነው፡፡ በዛሬው እለት ያደረጉት የመጨረሻ የልምምድ ፈተናም ክፍተቶቻቸውን ለይተው በማስተካከል ለዋናው ሀገር አቀፍ ፈተና እንዲዘጋጁ ያሚያደርጋቸው መሆኑን ተናግሯል፡፡   የመጨረሻው ልምምድ ለዋናው ፈተና ያደረኩትን ዝግጅት ለመፈተሽ ያስቻለኝ ነው ስትል የገለጸችው ደግሞ ተማሪ ዮርዳኖስ አበበ ነች፡፡   ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ ልምምዶችን እና በቂ ዝግጅት በማድረግ ሀገር አቀፍ ፈተናውን በመጠባበቅ ላይ መሆኑን የገለጸው ደግሞ ተማሪ አቤኔዘር ፍቃዱ ነው፡፡        
ዜጎች ደምና የዓይን ብሌን በመለገስ የሚያበረክቱትን በጎ ተግባር አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Jun 14, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ዜጎች ደምና የዓይን ብሌን በመለገስ የሚያበረክቱትን በጎ ተግባር አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ። ዓለም አቀፍ የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ በተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።   የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በመርሀ ግብሩ ላይ እንደገለፁት፤ በኢትዮጵያ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየዳበረ ሲሆን በህብረተሰቡ ዘንድም ደም መለገስ እየተለመደ ነው። ይሁን እንጂ ደም የመለገስ ተግባር ወጥነት እንደሌለው ያነሱት ዶክተር መቅደስ፤ በዘመቻና በንቅናቄ ተግባራት ላይ መመስረቱ ውስንነት እንዲያጋጥመው አድርጎታል ብለዋል። ህብረተሰቡ በራሱ ተነሳሽነት ደም የመለገስ ተግባርን ቀጣይነት ባለው መልኩ እንዲያከናውንም ጥሪ አቅርበዋል። ይህም በደም መፍሰስ ምክንያት የሚከሰት የእናቶች ሞት ለማስቀረት የሚደረገውን ጥረት ከዳር ለማድረስ አይነተኛ ሚና እንዳለው አመልክተዋል። በተለያየ የጤና እክል ምክንያት በቋሚነት ደም ለሚያስፈልጋቸው፣ በተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ አደጋ የደም እጥረት ለሚያጋጥማቸው ሰዎችም የደም አቅርቦት ወሳኝ በመሆኑ ደም የመለገስ ልምዱ እየተጠናከረ መሄድ እንዳለበት ጠቁመዋል። መንግስት የደም ባንኮችን፣ የህክምና ተቋማትንና መሰል ግብዓቶችን በማሟላት ረገድ እያከናወነ ባለው ተግባር አበረታች ውጤት መመዝገቡንም ገልጸዋል። የጤና አገልግሎትን ወጥና ተደራሽ ለማድረግ ዜጎች ደምና የዓይን ብሌን በመለገስ የሚያበረክቱትን አስተዋፅኦ አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ነው ዶክተር መቅደስ የገለጹት።   የኢትዮጵያ ደምና ሕብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አሸናፊ ታዘበው በበኩላቸው፤ አንድ ሰው ደምና የዓይን ብሌን በሚለግስበት ወቅት ተስፋን፣ የወደፊት ብርሀንና ህይወትን መስጠት መሆኑን አስታውቀዋል። ይህም ከስጦታዎች ሁሉ የላቀ ስጦታ መሆኑን ነው የገለጹት። በመረሀ ግብሩ ላይ በተከታታይ ደም የለገሱ ሰዎች እውቅና የተ ሰጣቸው ሲሆን፤ ሰዎች ከህልፈት በኋላ የዓይን ብሌንን እንዲለግሱ ጥሪ የሚቀርብበት ነውም ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰኔ ወር እየተከበረ ያለው 21ኛው የደምና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን "የሕይወትና የብርሀን ስጦታ! ደም ይለግሱ፤ ብሌንዎን ቃል ይግቡ" በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተከበረ ያለው።  
የትራፊክ አደጋን በተቀናጀ መንገድ ለመከላከል የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ - አገልግሎቱ
Jun 14, 2025 45
ድሬደዋ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፡- የትራፊክ አደጋን በተቀናጀ መንገድ ለመከላከል የተጀመሩ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የፌደራል የመንገድ ደህንነት እና መድን ፈንድ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ጀማል አባሦ ተናገሩ። የፌዴራልና የክልሎች የዘርፉ አመራሮች በምስራቅ የኢትዮጵያ ክፍሎች የትራፊክ አደጋን ለመከላከል እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን በመመልከት የዘርፉን አፈጻጸም በድሬዳዋ እየገመገሙ ነው።   በመርሃ ግብሩ የተሳተፉት የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጀማል አባሦ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ የትራፊክ አደጋ በሰውና በሀገር ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ነው። ችግሩን በተቀናጀ መንገድ ለመከላከል የ10 ዓመታት የተናበበ ስትራቴጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱን ጠቅሰው፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጁ ስራዎች ለውጥ ማምጣት መቻሉን አውስተዋል። ይህንን ለውጥ በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ አዳዲስ ዲጂታል ሪፎርሞች፣ ዘመናዊ አሰራሮችና ህጎች በመተግበር ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተለይ በምስራቅ ተጎራባች ክልሎች እየተገነቡ የሚገኙት የኮሪደር ልማቶች የትራፊክ ፍሰትን አስተማማኝ በማድረግ አደጋን ለማስቀረት ወሳኝ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው አንሰተዋል። እንደ ሀገር የተጀመረውን ዲጂታል የትራፊክ አደጋ የመከላከል ስራ በትክክል ዕውን በተደረገበት ድሬዳዋ መሠረታዊ ለውጥ ማምጣቱን ጠቅሰው ተሞክሮውን በማስፋት አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።   የድሬዳዋ አስተዳደር የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ባለስልጣን ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ሹክሪ አብዱረህማን በበኩላቸው፤ ባለስልጣኑ ከፍትህ እና ከትራፊክ ተቋማት ጋር ቅንጅት በመፍጠር አበረታች ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በተለይ ከትምህርት ቤቶችና ሌሎች ባለድርሻዎች ጋር የተቀናጀ የትራፊክ አደጋ የመከላከል ስራ በመሰራቱ አደጋው እየቀነሰ መምጣቱን ተናግረዋል። በምስራቅ ተጎራባች ክልሎች የተካሄደው የስራ ጉብኝት ለቀጣይ ስራ ጥሩ መደላድል እንደሚፈጥር በመግለጽ።  
ማህበሩ ለእናቶች ማቆያ አገልግሎት የሚውል የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
Jun 14, 2025 129
ባህርዳር፤ ሰኔ 7/2017 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በአማራ ክልል በደቡብ ጎንደርና ሰሜን ጎጃም ዞኖች ለሚገኙ ሁለት ጤና ጣቢያዎች ለእናቶች ማቆያ አገልግሎት የሚውል የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ። የማህበሩ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፈቃዱ ማዘንጊያ በድጋፍ ርክክቡ ወቅት እንደገለጹት ማህበሩ ግምታቸው 2 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የቁሳቁስ ድጋፉን ያስረከበው ለክልሉ ጤና ቢሮ ነው።   ድጋፉም በደቡብ ጎንደር ጋህሳይና በሰሜን ጎጃም ሳንክራ ጤና ጣቢያዎች ለተገነቡ የእናቶች ማቆያ ማዕከላት መሆኑንም ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል። ድጋፍ ከተደረጉት ቁሳቁስም አልጋዎች፣ የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች፣ የማብሰያ፣ የመመገቢያ ወንበሮችና ጠረጴዛዎች፣ ቴሌቪዥን፣ ብርድ ልብስ፣ ለምግብ አገልግሎት የሚውል ዱቄትና ሌሎችም ይገኙበታል።   ቀደም ሲልም ማህበሩ የእናቶችና ህፃናት ሞትን ለመቀነስ በክልሉ በዋግህምራ፣ ሰሜንና ደቡብ ወሎ እንዲሁም ሰሜን ሸዋ ዞኖች ለሚገኙ አምስት ጤና ተቋማት ተመሳሳይ ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል። እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ በአፋር፣ በትግራይ፣ በኦሮሚያና በሲዳማ ክልሎች ማህበሩ መሰል ድጋፎችን በማድረግ የእናቶችና ህፃናት ሞትን ለመቀነስ ሙያዊ ግዴታውን እየተወጣ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።   የክልሉ ጤና ቢሮ ተወካይ ዶክተር ቤተልሄም መኮንን እንዳሉት ማህበሩ በሁለት ጤና ጣቢያዎች ለተገነቡ የእናቶች ማቆያ ማዕከላት ያደረገው ድጋፍ የነበረውን የቁሳቁስ ችግር ሙሉ በሙሉ የቀረፈ ነው ብለዋል። ይህም ራቅ ካሉ አካባቢዎች የሚመጡ ነፍሰ-ጡር እናቶች በማቆያ ማዕከላቱ ሳይቸገሩ ተገቢውን አገልግሎትና የባለሙያ ክትትልና ድጋፍ አግኝተው እንዲወልዱ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። ማህበሩ የእናቶችና ህፃናት ሞትን ለመቀነስ እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ እያደረገ ያለው የቁሳቁስ ድጋፍ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ቢሮው አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ያደርጋል ብለዋል። ''ለጋህሳይ ጤና ጣቢያ የእናቶች ማቆያ የተደረገው የቁሳቁስ ድጋፍ የነበረውን ችግር ሙሉ በሙሉ የቀረፈ ነው'' ያሉት ደግሞ የደቡብ ጎንደር ዞን ጤና መምሪያ ተወካይ ኃላፊ አቶ ኃይለኢየሱስ ዳኘው ናቸው። በክልሉ ከተገነቡ 727 የእናቶች ማቆያ ማዕከላት 544ቱ በአሁኑ ወቅት የተሟላ አገልግሎት ለነፍሰ-ጡር እናቶች እየሰጡ እንደሚገኙም ከክልሉ ጤና ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።  
ኢኮኖሚ
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደህንነትን በማረጋገጥ ለግንባታው አስተዋጽኦ እያደረግን ነው - የመከላከያ ሠራዊት አመራሮችና አባላት
Jun 14, 2025 73
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ደህንነትን በማረጋገጥ ለግንባታው በተለያየ መልኩ አስተዋጽኦ እያደረገን ነው ሲሉ የመከላከያ ሠራዊት አመራሮችና አባላት ገለጹ። የመላው ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት ታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ደረጃ ላይ መድረሱ እንዳስደሰታቸውም ተናግረዋል። በምዕራብ ዕዝ የ404 ሕዳሴ ኮር ሶስተኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን "ሕዳሴን በሕዳሴ ኮር" በሚል መሪ ሐሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች በማክበር ላይ ይገኛል። የሠራዊቱ አባላትም በዛሬው ዕለት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም የመላው ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ደረጃ ደርሶ በመመልከታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።   የምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ሙላቱ ጀልዴ በጉብኝቱ ወቅት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ደረጃ ለመድረሱ መላው ኢትዮጵያውያን ያላሰለሰ ጥረት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። መከላከያ ሠራዊቱ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እውን እንዲሆን የግድቡን ደህንነት ከማስጠበቅ ጀምሮ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸዋል።   በምዕራብ ዕዝ የሪጅን ሶስት ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ዘመኮንን አበራ እንደገለጹት፤ ሠራዊቱ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ግዳጁን በብቃት ለመወጣት ከምን ጊዜውም በላይ ዝግጁ ነው። ሕዳሴ ኮር የግድቡን አካባቢ ሰላምና ጸጥታ ለማስከበር እያደረገ ያለውን ተግባር በውጤታማነት እየተወጣ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህንን ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   በምዕራብ ዕዝ የ403 ኮር አባል ሌተናል ኮሎኔል ፍሰሃ ጥላሁን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የታላቁ የህዳሴ ግድብ የመላው ኢትዮጵያውያን እስትንፋስ በመሆኑ ሠራዊቱ ሁሌም የአካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ታላቁ የሕደሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ ሠራዊቱ አስፈላጊውን ሁሉ ማበርከቱን ጠቁመዋል። ዛሬ ለደረሰበት የመጠናቀቅ ደረጃ ደርሶ በመመልከታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።   በምዕራብ ዕዝ የ403 ኮር አባል ሌተናል ኮሎኔል ቴዎድሮስ ዘመነ እንዳሉትም፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የይቻላል መንፈስ ማሳያ ነው። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ለሀገር በረከት የመሆን ደረጃ ላይ በመድረሱ መደሰታቸውን ጨምረው ተናግረዋል።
ሴቶች በኮንስትራክሽን ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ ነው
Jun 14, 2025 46
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ ሴቶች በኮንስትራክሽን ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን አስታወቀ። ኮርፖሬሽኑ ”ኢትዮጵያ ትገንባ” በሚል መሪ ሀሳብ ሴቶች በኮንስትራክሽን ዘርፉ ያላቸው ተሳትፎ ማዳበር በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ የሚመክር ኮንፍረንስ ተካሂዷል።   በመድረኩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሴት አመራሮች እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ፅህፈት ቤት ሃላፊ ቤዛዊት ግርማ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያ ሴቶች በተለያዩ የግንባታ ፕሮጀክቶችና መሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎች ጉልህ ሚና እየተወጡ ይገኛሉ። በአሁኑ ወቅትም ዘርፉ በቴክኖሎጂ እያደገ በመምጣቱ በአገሪቱ የልማት ጉዞ ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። ኮርፖሬሽኑ በተለያዩ ህጎች ላይ ማሻሻያዎችን በማድረግና ስትራቴጂዎችን በመንደፍ ሴቶች በዘርፉ ያላቸውን ተሳትፎ ከፍ ለማድግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ሴቶች በግንባታ ዘርፍ ያለውን እድልና ቴክኖሎጂ በመጠቀም እውቀታቸውንና ክህሎታቸውን በማዳበር ወደ ዘርፉ በስፋት መግባት እንዳለባቸውም አስታውቀዋል። ሴቶች በኮንስትራክሽን ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ነው ዶክተር ቤዛዊት ያስታወቁት።   የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ፍቅር አባይ በዚሁ ግዜ በአገሪቱ በሚከናወኑ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል ። ይህንንም ለማጠናከር የህግና ፖሊሲ ክፍተቶች ከመሙላት አኳያ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልገው ጠቁመዋል።   በኮንስትራክሽን ስራ ላይ የተሰማሩ መንግስታዊና የግል ድርጅቶችም የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ወሳኝ ድርሻ አላቸው ያሉት ደግሞ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ነጭቴ ፍላቴ ናቸው። የሴቶችን እኩል ተሳታፊነት የተመለከቱ ረቂቅ አዋጆች ፀድቀው ወደ ስራ እንዲገቡ የድርሻቸው እንደሚወጡም ተናግረዋል።   ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና በመድረኩ ጥናት ያቀረቡት ደጅይጥኑ አለነ እንዳሉት ሴቶችን በኮንስትራክሽን ዘርፍ ያላቸው ተሳትፎ ለማሳደግ አቅዶ መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል። በሀገሪቱ እየተከናወኑ በሚገኙ የኮሪደር ልማት የሴቶች ተሳትፎ የተሻለ በመሆኑ ይህም ለሌሎች ዘርፎች ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።    
ኢትዮጵያ የምታስተናግዳቸው ኮንፍረንሶች መልካም ገጽታን ከማስተዋወቅ ባሻገር የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን ለማጠናከር የሚያግዙ ናቸው
Jun 14, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የምታስተናግዳቸው አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ኮንፍረንሶች የሀገሪቱን መልካም ገጽታ ከማስተዋወቅ ባሻገር የዲፕሎማሲ ግንኙነትን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚያግዙ ተገለጸ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ በርካታ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ኮንፍረንሶች በስፋት እየተካሄዱ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ ከተማን የዲፕሎማቲክ መቀመጫነትና የአፍሪካ መዲናነት የሚመጥኑ መሰረተ ልማቶች መሟላት ደግሞ ለኮንፍረንስ ቱሪዝም መበራከት ምቹ ሁኔታን የፈጠሩ ናቸው። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የተለያዩ ዘርፎች ለውጭ ባለሃብቶች ክፍት መደረጉም ሌላው እድል ነው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችም ይህንኑ ነው የሚያረጋግጡት።   በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ አማረ ቀናው(ዶ/ር)፤ ከተማዋ የምታስተናግዳቸው ዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ስብሰባዎች ከሀገር በጎ ገጽታ ግንባታ ያለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አላቸው። የኢትዮጵያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና የዲፕሎማሲ ስራ ለሀገር ወስጥም ሆነ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማድረስ እንደሚያግዙ ተናግረዋል።   በቱሪዝም ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን መሪ ስራ አስፈጻሚ አለማየሁ ጌታቸው፤ ኢትዮጵያ እየገነባቻቸው ያሉ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችና የቱሪዝም መስህቦቿ ለኮንፍረንስ ቱሪዝም ተመራጭ እንዳደረጓት ይገልጻሉ። የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና የሌሎች መሰረተ ልማቶች መሟላት አዲስ አበባን ለኮንፍረንስ ቱሪዝም የበለጠ ምቹና ተመራጭ እንድትሆን ማስቻላቸውን ተናግረዋል። ወደ ሀገሪቱ የሚመጡ የውጭ ዜጎች ስለኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻዎችና ባህላዊ እሴቶች በቂ ግንዛቤ እንዲይዙ በሚካሄዱ ኮንፍረንሶች ገለጻ እየተደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል።   በኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት ከተካሄዱ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ኮንፍረንሶች አራቱ በኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ የጉባዔው ጠቅላይ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ናቸው። እርሳቸው እንደሚሉት፤ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፎ ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ተሳትፎ የበለጠ ለማሳደግ ኮንፍረንሶቹ ዕድል የፈጠሩ ናቸው ብለዋል።   የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላት ዳይሬክተር ሳሚናስ ሰይፋ፤ ተቋሙ በቅርቡ ዓለም አቀፉን የአይዲ ፎር አፍሪካ ጉባዔ በተሳካ ሁኔታ ማካሄዱን አስታውሰዋል። የተለያዩ ኮንፍረንሶችን ለመሳተፍ የሚመጡ እንግዶችን የቆይታ ጊዜ የሚያራዝሙ በርካታ ሥራዎች መሰራታቸውንና በቱሪዝም ዘርፍ የተሻለ አቅም መፈጠሩንም ተናግረዋል። በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ አማረ ቀናው(ዶ/ር) በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ ኮንፍረንሶቹ ላይ የሚነሱ ሀሳቦች ለፖሊሲ ግብዓት እንዲሆኑ የኮንፍረንሶቹን ጭብጦች በህትመት መልክ እንዲሰራጩ የሚያደርግ መሆኑንም ተናግረዋል።
የወጣቶችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ተግባራትን ይበልጥ ማጠናከር ይገባል - ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀስላሴ
Jun 14, 2025 79
ጊንጪ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የወጣቶችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ተግባራትን ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ጊንጪ ከተማ አቅራቢያ የተገነባው 'ኬኛ ቢቨሬጅስ' ፋብሪካ ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓት ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሸመልስ አብዲሳን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።   በዚህ ወቅት ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፤ የልማት ስራዎች የወጣቱን ተጠቃሚነት ማዕከል ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው ተናግረዋል። ዛሬ የተመረቀው ፋብሪካም ለአካባቢው ማህበረሰብ ትልቅ በረከት መሆኑን ጠቅሰው፤ ከጥሬ እቃ አቅርቦት ጀምሮ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አለውም ብለዋል። በተለይ የግብርና ዘርፉን ከማሳደግ አንጻር ፋይዳው የጎላ መሆኑን አንስተዋል። ይህም በመሆኑ ለወጣቶች ስራ የሚፈጥሩ እና የወጣቱን ተጠቃሚነት ማዕከል ያደረጉ የልማት ተግባራትን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል።   የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የልማት ተግባራት ወጣቶችን በስፋት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት አሰራሮችን በማሻሻል እና ህዝቡን በስፋት በማሳተፍ አበረታች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። በክልሉ ያለውን የልማት አቅም በመጠቀም የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አንስተዋል። በተለይም ወጣቶች ስራ እንዲያገኙና በንቃት እንዲሳተፉ ዕድል የፈጠሩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   ዛሬ የተመረቀው ፋብሪካ የዚሁ ጥረት ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፤ መሰል ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። ፋብሪካው በክልሉ ምዕራብ ሸዋ ዞን በ110 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፤ 22 ቢሊዮን ብር ኢንቨስት የተደረገበት መሆኑም ታውቋል። ፋብሪካው ከ4ሺህ በላይ ባለአክሲዮኖች የተቋቋመ፣ ከ250 ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ያገኙበትና እና በእሴት ሰንሰለቱ መሰረት ለ1ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥር ተመልክቷል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
መገናኛ ብዙሃን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በመታገዝ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር መስራት ይገባቸዋል
Jun 14, 2025 98
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በመታገዝ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር መስራት እንዳለባቸው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ገለጹ። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና እሁድ ኤ.አይ ስቱዲዮ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አሰራር ጥበብ ያሰለጠኗቸውን 25 የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች አስመርቀዋል።   ሰልጣኞቹ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የተውጣጡ ናቸው። የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎቹ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ በመታገዝ በይዘት ስራዎች ላይ እሴት መጨመር የሚያስችል የጽንሰ ሃሳብና የተግባር ተኮር ስልጠና የወሰዱ ናቸው። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በምርቃት መርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ ስልጠናው በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚወስድ ነው። በመሆኑም ሰልጣኞች የተማሩትን ወደ ተግባር በመለወጥ ሀገርን ለመቀየር የመስራት ሃላፊነት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር፣ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር፣ የወል ትርክትን ለመፍጠርና ሀገርን ለማበልጸግ የተያዙ ዋና ዋና እቅዶችን ለማሳካት ቴክኖሊጂውን ጥቅም ላይ በመዋል መስራት ይገባል ብለዋል። በተመሳሳይ በተማሩበት ሙያ ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ፊልሞችን በማምረት፣ ሌሎች ሙያተኞችን በማሰልጠን፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ጽንሰ ሃሳብን ግንዛቤ በመፍጠር መስራት እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል። የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የደረሰበትን ደረጃ በመረዳትና በመገናኛ ብዙሃን የይዘት ስራዎች ውስጥ በመጠቀም ለህብረ ብሔራዊ አንድነት ማጠናከርና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር ማዋል እንደሚገባ በአጽኖኦት አንስተዋል። የመገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችም ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ እውቀት እንዲስፋፋ መስራት እንዳለባቸው በማስገንዘብ ተቋማትን በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች የማዘመን ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።   የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ በበኩላቸው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአግባቡ መጠቀም በድህረ እውነት በሀገር ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከል ይረዳል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት እየተሰራ ለሚገኘው የአሰባሳቢ ትርክት ግንባታም አጋዥ መሆኑን ጠቅሰው፤ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የፈጠራ ስራዎችን ለመደገፍ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።   የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ኢ/ር ዶ/ር) በበኩላቸው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እንደ ሀገር ትልቅ ለውጥ ማምጣት ይቻላል ብለዋል። ኢትዮጵያ ዓለም ከደረሰበት የቴክኖሎጂ ደረጃ ጋር ለመሄድ በርካታ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን ጠቁመው፤ መገናኛ ብዙሃንም ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።   በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የወሰዱት ስልጠና ለይዘትና ሌሎች ስራዎች ትልቅ አቅም በመፍጠር የሀገርን ጥቅም ለማስጠበቅ ፋይዳው ትልቅ መሆኑንም የመገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎች ተናግረዋል።   በመሆኑም በተቋሞቻቸው በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የታገዙ ስራዎችን ለመስራት ምቹ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥሩ አረጋግጠዋል። ሰልጣኞቹ በበኩላቸው በስልጠናው ያገኙትን እውቀት የሀገራቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ እንደሚያውሉ ገልጸዋል።
ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ከዓለም ፈጣን የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር የሚያወዳድር ነው
Jun 14, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ በሳይንስ ሙዚየም የተከፈተው ቋሚ ኤግዚቢሽን ኢትዮጵያን ከዓለም ፈጣን የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር የሚያወዳድርና የትውልዱን መጻዒ ዕድል በፈጠራና ምርምር የሚያግዝ መሆኑን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽንን በይፋ ከፍተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገን መስራት፣ ማየት እና መለማመድ የሚፈልጉ ሰዎች በሙሉ የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽንን እየመጡ መመልከት አለባቸው ብለዋል። ኢትዮጵያውያን ነገን መስራት ነገን መለወጥ ከፈለጉ ልጆቻቸውን ወደ ኤግዚቢሽኑ ሊያመጧቸው እንደሚገባም አመልክተዋል። ልጆቻችንም ይህ ትልቅ ዕድል እንደሆነ ተገንዝበው ክረምቱን ይህንን ቋሚ ኤግዚቢሽን በማየት ብዙ ትምህርት መቅሰም አለባቸው ሲሉም ገልጸዋል። ኤግዚቢሽኑ በውስጡ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የአካባቢ፣ የግብርና፣ የውሃና ኢነርጂ፣ የስፔስና አቪየሽን ማሳያ ክፍሎችን አካቷል። በዕለቱ ቋሚ ኤግዚቢሽኑን የቱሪዝም፣ የኪነ ጥበብ፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና ታዋቂ ግለሰቦች ጎብኝተውታል። አስተያየታቸውን የሰጡ ጎብኚዎችም ኢትዮጵያ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ባከናወነቻቸው ሥራዎች መደመማቸውን ነው ያነሱት። የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ነጋ ወዳጆ ቴክኖሎጂን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ምን ያህል ውጤታማ ሊያደርግ እንደሚችል ያየንበት ነው ብለዋል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርትና በሌሎች ዘርፎች አጋዥ በመሆኑ ትውልዱ ሳይንስን በአግባቡ በመረዳት ለአዳዲስ ፈጠራዎች እንዲተጋ የሚያግዝ መሆኑንም አመልክተዋል።   የፍሎውረስ ኢቨንትስ ስራ አስኪያጅ ዮአዳን ጥላሁን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የቋሚ ኤግዚቢሽኑ መከፈት ተማሪዎች ሳይንስ ላይ የተመሰረተ ተጨባጭ ፊልምና ትርኢት የማየት ዕድል እንዲያገኙና ከቴክኖሎጂ ጋር በደንብ እንዲተዋወቁ ያስችላል። በቋሚ ኤግዚቢሽኑ ኢትዮጵያን በዓለም ተወዳዳሪ የሚያደርጉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን አይቻለሁ የሚሉት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ረዳት መምህር ማስተር ምህረት ከድር ናቸው።   ጋዜጠኛ አስካለ ተስፋዬ በበኩሏ፤ በሳይንስ ሙዚየም በቴክኖሎጂ የታገዘ የፈጠራ ትርኢትና ፊልም በአድናቆት መመልከቷን ገልጻለች። ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ትልቋ ኢትዮጵያን ከማሳየት ባለፈ የተፈጥሮ ጸጋ፣ የእድገትና የቴክኖሎጂ ልህቀት መሻቷን የሚያሳይ እንዲሁም ለተማሪዎች የነገ ተስፋ ለተመራማሪዎች ደግሞ ምቹና ሁሉን ያቀፈ ማዕከል መሆኑን ነው ያብራራችው።   ጋዜጠኛ ዮናስ ከበደ በሙዚየሙ የትናንት፣ የዛሬና የነገ ማንነታችንን ያየንበት ነው ብሏል። ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት ከፍታ ትናንትን ያልረሳና ትውልድን ያስተሳሰረ መሆኑ ሁሉንም የሚያኮራ መሆኑን በማንሳት።   ጋዜጠኛ ዳዊት አበበም የሰው ሰራሽ አስተውሎት የሰው ልጆችን ህይወት በማቅለል በኩል የደረሰበትን ደረጃ በቀላሉ ማየትና በዚያ መጠቀም የሚያስችሉ ዕድሎች መፈጠራቸውን አድንቋል።   የሳይንስ ሙዚየምን በሰለጠኑ ሀገራት የመመልከት ዕድል እንደነበረውና በአጭር ጊዜ በኢትዮጵያ እውን ሆኖ ማየቱ አግራሞት እንደፈጠረበት የገለጸው ደግሞ አርቲስት ዳንኤል ተገኝ ነው። በሙዚየሙ ያገኘውን ዕድል ተጠቅሞ ለሀገርና ህዝብ ጠቃሚ የሆነ ፊልም ለመስራት ፍላጎት አንዳደረበት ጠቅሷል።   በቋሚ ኤግዚቢሽኑ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የህዋ ቅርጽ ሉላዊ የትዕይንት አዳራሽ ይፋ የተደረገ ሲሆን ስለ-ህዋ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው እጅግ አስደማሚ ምስሎችን በማቅረብ የህዋውን አለም እጅግ አቅርቦ ያሳያል።
የበረሃ አንበጣና ፀረ ተባይ መከላከያ ቴክኖሎጂን በስፋት በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ ነው - ኮርፖሬሽኑ
Jun 14, 2025 54
አዳማ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የበረሃ አንበጣና ፀረ ተባይ መከላከያ ቴክኖሎጂን በስፋት በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ገለፀ። ኮርፖሬሽኑ ከናሽናል ኤርዌይስና ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በመሆን በቀጣይ የርጭት አውሮፕላን አገልግሎት ተደራሽነትን ማስፋትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችለውን ውይይት በአዳማ ከተማ አካሂዷል።   የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ፈለቀ ገዛኸኝ በወቅቱ እንደገለፁት የበረሃ አንበጣን ከመከላከል ባለፈ የሰብል ምርትና ምርታማነትን የሚቀንሱ ተባዮች ለማጥፋት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ ነው። ኮርፖሬሽኑ የራሱ በሆነ 10ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በ22 የሰብል ዓይነቶች ምርጥ ዘር እያባዛ መሆኑን ተናግረዋል። ኮርፖሬሽኑ አሁን ላይ ተጨማሪ 5ሺህ ሄክታር መሬት ወደ እርሻ በማስገባት የተለያዩ የሰብል ምርጥ ዘሮችን በጥራትና በብዛት ለማምረት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ከናሽናል ኤርዌይስ ጋር በመተባበር በ6ሺህ ሄክታር ላይ የለሙ የተለያዩ የምርጥ ዘር ሰብሎች በአረም፤ በተባይና በሌሎች ተያያዥ የሰብል በሽታዎች እንዳይጎዱ በአውሮፕላን ርጭት መካሄዱን ለአብነት ጠቅሰዋል።   የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ምክትል ስራ አስኪያጅ ጫላ አበበ በበኩላቸው ኢንተርፕራይዙ ከ32ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ60 በላይ የሰብል ዝርያዎችን በማልማት የምርጥ ዘር ፍላጎትን ለማሟላት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንተርፕራይዙ በ2016/17 ምርት ዘመን ከ800ሺህ ኩንታል በላይ የተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ምርጥ ዘር ማምረቱን ጠቅሰው የፀረ አረምና ፀረ ሰብል በሽታ ማጥፊያ የርጭት አውሮፕላን በመጠቀሙና የሰብል እንክብካቤ ስራ በመስራቱ ከ160ሺህ ኩንታል በላይ ተጨማሪ ምርት ማግኘት መቻሉን አስታውቀዋል። ድርጅቱ በዋናነት በምስራቅ ባሌና ባሌ፣ በአርሲና ምዕራብ አርሲ ዞኖች የስንዴ ልማት እንዲሁም በወለጋ በበቆሎ ምርጥ ዘር ላይ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ኢንተርፕራይዙ በተለይ ከናሽናል ኤርዌይስ ጋር በመተባበር የምርጥ ዘር ብዜት ውጤታማነትን አሁን ካለበት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። በ2017/18 የምርት ዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለንን ቅንጅት በማጠናከር ምርታማነትን በተሻለ ደረጃ ለማሳደግ አቅደን እየሰራን ነው ሲሉም አክለዋል።   የናሽናል ኤርዌይስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ካፒቴን አበራ ለሚ በበኩላቸው ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የበረሃ አንበጣን ጨምሮ የአውሮፕላን ፀረ ተባይና ፀረ መድኃኒቶች ርጭት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የግብርና ዘርፍ ዕድገት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የማቅረብ ስራ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በቀጣይም በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ከኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ጋር ተፈራርመዋል።
ለከተማዋ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ባለሙያዎች እያፈራን ነው- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 14, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ለሰው ሃይል ልማት ቅድሚያ ሰጥተን በመስራታችን ለአዲስ አበባ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ባለሙያዎች እያፈራን እንገኛለን ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ “ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን 15ኛውን ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ አውደ ርዕይ መርቀው ከፍተዋል።   አውደ ርዕዩ ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ቀን ክፍት ሆኖ አንደሚቆይ ተገልጿል፡፡ ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ኢትዮጵያ በርካታ የልማት ተግባራትን በማከናወን የብልጽግና መሰረት እየጣለች ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ የምትበለጽገው የራሳችንን የሰው ሀይልና የተፈጥሮ ሀብት አቀናጅተን በማልማት ነው በሚል ጽኑ አቋም በሰራናቸው ስራዎች የብልጽግና መሰረት እየተጣለ ይገኛል ብለዋል። በዚህም አዲስ አበባን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ የከተማ አስተዳደሩ ቀን ከሌት በትኩረት እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት፡፡ እየተከናወኑ ባሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ከፍተኛ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ በሰው ሃይል ልማት ላይ በተሰራው ስራ በከተማዋ ልማት አሻራቸውን ያሳረፉ ባለሙያዎችን ማፍራት መቻሉን አንስተዋል፡፡   የቴክኒክና ሙያ ዕውቀትን የቀሰሙ ባለሙያዎች ለከተማዋ ልማት ትልቅ እገዛ የሚያደርጉ የተለያዩ ችግር ፈቺ ማሽኖችን እያመረቱ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ለኮሪደር ልማቱ ብቁ የሰው ሃይል በማቅረብና የተለያዩ ማሽኖችን በማምረት ያበረከቱትን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለአብነት አንስተዋል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ጥራት ያለው ተኪ ምርት በማምረት ከውጭ የሚገባ ምርትን በማስቀረት ረገድ የራሳቸውን ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከንቲባዋ በዘርፉ የሚነሱ ጥያቄዎችን በመፍታት እና የሚደረገውን ድጋፍ በማጠናከር የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ሚና የበለጠ እንዲጠናከር ይደርጋል ብለዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው ከተማ አስተዳደሩ ባለፉት ሰባት አመታት ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ ተቋማቱን በወርክሾፕ፣ በመሰረተ ልማት፣ በማሽነሪ እና በሰው ሃይል የማጠናከር ስራ ማከናወኑን አስታውቀዋል። በተሰራው ውጤታማ ስራ ኮሌጆቹ ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ሙያ የሚቀስሙባቸው ተቋማት ለመሆን መብቃታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ አውደ ርዕዩ ህብረተሰቡ በዘርፉ የተፈጠረውን አቅም እንዲገነዘብ ለማድረግ የተዘጋጀ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በአውደ ርዕዩ ከ150 በላይ የፈጠራ ውጤቶች ለእይታ የሚቀርቡ ሲሆን የፓናል ውይይቶችና ሌሎች መርኃ ግብሮች እንደሚካሄዱ ተመላክቷል።
ስፖርት
የመጀመሪያው የፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ ዛሬ ይጀመራል
Jun 14, 2025 55
አዲስ አበባ ሰኔ 7/2015(ኢዜአ):- የመጀመሪያው የፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ በአሜሪካ አስተጋጅነት ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል። በምድብ አንድ የሚገኙት አል አህሊ ከኢንተር ሚያሚ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት በሚያሚ ሀርድ ሮክ ስታዲየም የመክፈቻ ጨዋታውን ያደርጋሉ። እ.አ.አ በ2000 የተጀመረው ውድድር (ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ) ከዚህ ቀደም አህጉራዊ የክለቦች ውድድርን ያሸነፉ ክለቦች የሚሳተፉበት ነበር። ዓለም አቀፉ የፊፋ በአዲስ መልክ ባስተዋወቀው አሰራር መሰረት ነባሩን ፎርማት በመሻር የተሳታፊ ክለቦችን ቁጥር ወደ 32 አሳድጓል። በዚሁ መሰረት ቡድኖቹ በስምንት ምድብ ተከፍለው ለአራት ሳምንታት 63 ጨዋታዎች በ11 የአሜሪካ ከተሞች ያደርጋሉ። በምድብ አንድ አል አህሊ፣ ኢንተር ሚያሚ፣ ፓልሜራስ እና ፖርቶ፣ በምድብ 2 አትሌቲኮ ማድሪድ፣ ቦታፎጎ፣ ፒኤስጂ እና ሲያትል ሳውንደርስ፣ በምድብ 3 ኦክላንድ ሲቲ፣ ባየር ሙኒክ፣ ቤኔፊካ እና ቦካ ጁኒየርስ፣ በምድብ 4 ቼልሲ፣ ኤስፔራንስ፣ ፍላሚንጎ እና ሎስ አንጀለስ ኤፍሲ ይገኛሉ።   በምድብ አምስት ሪቨር ፕሌት፣ ኡርዋ ሬድ ዳይመንድስ፣ ሞንትሬይ እና ኢንተር ሚላን፣ ምድብ 6 ፍሉሜንሴ፣ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ፣ ኡልሳን እና ማሜሎዲ ሳንዳውንስ፣ ምድብ 7 ማንችስተር ሲቲ፣ ዋይዳድ ካዛብላንካ፣ አል አይን እና ጁቬንቱስ፣ በመጨረሻው ምድብ 8 ሪያል ማድሪድ፣ አል ሂላል፣ ፓቹካ እና ሬድ ቡል ሳልበዝርግ ተደልድለዋል። በክለቦች የዓለም ዋንጫ ላይ ከአውሮፓ፣ ደቡብ አሜሪካ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ አፍሪካ ፣ ማዕከላዊ አሜሪካ፣ ካሪቢያን እና ኦሺንያ ቀጣናዎች የሚገኙ ክለቦች ይሳተፋሉ። ፊፋ አህጉራት ባላቸው ወቅታዊ ብቃት እና ውጤት መሰረት ለአውሮፓ 12 (ዩኤፋ) ፣ ለደቡብ አሜሪካ (ኮንቤሞል) ስድስት፣ እስያ (4(፣ አፍሪካ (4) እና ሰሜን አሜሪካ ፣ ማዕከላዊ አሜሪካ እና ካሪቢያን (ኮንካካፍ) በተመሳሳይ አራት አግኝተዋል። አሜሪካ በአዘጋጅነቷ እና ኦሽንያ ባላት አህጉራዊ የክለብ ውጤት በተመሳሳይ አንድ አንድ የተሳትፎ ኮታ አግኝተዋል። ፊፋ ለውድድሩ ተሳታፊዎች የአንድ ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽልማት አዘጋጅቷል። የፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ እስከ ሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
የኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ 50ኛው የፕሪሚየር ሊግ የደርቢ ጨዋታ ይጠበቃል
Jun 14, 2025 53
አዲስ አበባ ሰኔ 7/2015(ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ35ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚያደርጉት ተጠባቂ ጨዋታ ዛሬ ይጀመራል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከቀኑ 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይካሄዳል። በደረጃ ሰንጠረዡ ኢትዮጵያ ቡና በ55 ነጥብ 2ኛ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ45 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። በአሰልጣኝ ነጻነት ክብሬ የሚመራው ኢትዮጵያ ቡና በፕሪሚየር ሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው 32 ጨዋታዎች 16 ጊዜ ሲያሸንፍ 8 ጊዜ ተሸንፎ፤ 8 ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይቷል። በ32ቱ ጨዋታዎች 28 ግቦችን ሲያስቆጥር 16 ጎሎችን አስተናግዷል።   ተጋጣሚው ቅዱስ ጊዮርጊስ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው 32 ጨዋታዎች በ12ቱ አሸንፎ 11 ጊዜ ተሸንፏል። 9 ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥቷል። ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ በፕሪሚየር ሊጉ እርስ በእርስ ሲገናኙ የዛሬው ለ50ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም 49 ጊዜ ተጫውተው ቅዱስ ጊዮርጊስ 21 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ኢትዮጵያ ቡና 8 ጊዜ ድል ቀንቶታል። 20 ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። በ45ቱ ጨዋታዎች በድምሩ 95 ጎሎች የተቆጠሩ ሲሆን ፈረሰኞቹ 63 እንዲሁም ቡናማዎቹ ደግሞ 32 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኢትዮጵያ ቡና የሊጉን ዋንጫ አንድ ጊዜ ያነሳ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ 16 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። በሊጉ ኢትዮጵያ ቡና መልካም የሚባል ጊዜን ያሳለፈ ሲሆን በአንጻሩ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚፈለገው የብቃት ደረጃ ላይ አልተገኘም። የሁለቱ ክለቦች በርካታ ደጋፊዎች ለጨዋታው ድምቀት ይሰጡታል ተብሎ ይጠበቃል። ቡድኖቹ በመጀመሪያው ዙር በሊጉ ባደረጉት ጨዋታ ያለ ምንም ግብ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው። ምሽት 12 ሰዓት ሻምፒዮንነቱን አስቀድሞ ያረጋገጠው ኢትዮጵያ መድን ከሀድያ ሆሳዕና ጋር ይጫወታሉ። ኢትዮጵያ መድን በ67 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ሲቀመጥ ሀድያ ሆሳዕና በ47 ነጥብ 5ኛ ደረጃን ይዟል።
አካባቢ ጥበቃ
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችንና ስነ ምህዳርን መሰረት ያደረገ ተከላ ለማካሄድ ዝግጅት ተደርጓል
Jun 14, 2025 52
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችንና ስነ ምህዳርን መሰረት ያደረገ ተከላ ለማካሄድ ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ። በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈፃሚ ፋኖሴ መኮንን ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በቂ ዝግጅት ተደርጓል። በመርሃ ግብሩ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ መትከል የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ገልጸው፤ ለሀገር በቀልና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ላላቸው ችግኞች ትኩረት መሰጠቱንም ጠቁመዋል።   የችግኝ ተከላ ሂደቱም ስነ-ምህዳርን መሰረት ያደረገ እንደሚሆን ጠቅሰው፤ ለዚህም አስፈላጊ የሆኑ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። ባለፉት አመታት ከተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች መገኘታቸውን ያነሱት መሪ ስራ አስፈጻሚው ይህም አሁን ላይ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እና የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።   የጉለሌ እጽዋት ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ጉተማ ሞረዳ በበኩላቸው፤ አዲስ አበባ ከተማን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የአረንጓዴ አካባቢ ሽፋንን ማሳደግ ወሳኝ ነው። ይህም የአየር ብክለትን ለመከላከል ጉልህ ሚና እንዳለው አንስተው፤ ለዚህም ሀገር በቀል እጽዋት ተመራጭ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርም በማዕከሉ ከተዘጋጁት ችግኞች 50 በመቶ የሚሆኑት ሀገር በቀል ዝርያ ያላቸው ናቸው ብለዋል።    
የሸገር ከተማ የመኖሪያ ብቻ ሳይሆን የማምረቻ ከተማ እንዲሆን በተከናወኑ ስራዎች ውጤት እየተገኘ ነው - ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)
Jun 12, 2025 99
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፡- የሸገር ከተማ የመኖሪያ ብቻ ሳይሆን የማምረቻ ከተማ እንዲሆን በተከናወኑ ስራዎች ውጤት እየተገኘ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ተናገሩ። በሸገር ከተማ አስተዳደር መነ አቢቹ ክፍለ ከተማ የአፕል ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የአስተዳደሩ አመራሮች፣ የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና ነዋሪዎች በተገኙበት ተካሄዷል።   በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)፣ ከተማው ከተመሰረተ ጀምሮ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ከተማዋ የመኖሪያ ብቻ ሳትሆን የማምረቻ ማዕከል እንድትሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። ከተማውን የዘመናዊ ግብርና ማዕከል ለማድረግ ባለፉት ዓመታት ከ10 ሺህ በላይ የማምረቻ ሼዶች ተገንብተው ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል መፈጠሩን ገልጸዋል። በሼዶቹ ውስጥ ሰፋፊ የዶሮ እርባታ ስራዎች፣ የወተት ላሞች እርባታ፣ በስጋ እንስሳት ማድለብና በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል። በተያዘው ክረምትም በከተማ አስተዳደሩ በ1 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፕልና አቮካዶ ችግኝ እንደሚተከል ገልጸው ዛሬም በመነ አቢቹ ክፍለ ከተማ በ38 ሄክታር መሬት ላይ የአፕል ችግኝ መተከሉን ተናግረዋል።   የሸገር ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የግብርና ክላስተር አስተባባሪ አቶ ግርማ ሀይሉ፣ በከተማ አስተዳደሩ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። በዚህ ክረምትም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያግዝና ለውጭ ገበያ የሚውሉ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች ይተከላሉ ብለዋል። ከሚተከሉት የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች መካከል ከ50 በመቶ በላይ የሚሆነው የአፕል ችግኝ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የሸገር ከተማ አስተዳደር መነ አቢቹ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ሆርዶፋ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው በዚህ ክረምት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል አስፈላጊ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ተናግረዋል። በክፍለ ከተማው በአጠቃላይ በ50 ሄክታር መሬት ላይ ከ50 ሺህ በላይ የአፕል ችግኝ ተከላ መጀመሩን ገልጸው የአካባቢው አርሶ አደርም መልካም ተሞክሮ እየወሰደ የተተከለውን ችግኝ እንዲንከባከብም አሳስበዋል።   በችግኝ ተከላው ላይ ከተሳተፉ የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል አቶ መስፍን መላኩ፣ በክረምቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።   በተከላው ተሳትፎ ያደረጉት የአፕል ችግኝ ጠቀሜታው ትልቅ መሆኑን በመገንዘብ መሆኑን ተናግረው በአካባቢው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሊጠናከር እንደሚገባም አመልክተዋል።    
በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በተለይም በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች የተሻለ ርጥበት ይኖራቸዋል - ኢንስቲትዩቱ
Jun 12, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በተለይም በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች የተሻለ የርጥበት ሁኔታ እንደሚኖራቸው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረውን የአየር ትንበያ አስመልክቶ ለኢዜአ በላከው መግለጫ በሚቀጥሉት ቀናት የሚኖረው የአየር ሁኔታ ለእርሻ ስራ እንቅስቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው አመላክቷል። ከዚህም ጋር ተያይዞ በምዕራብ እና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚጠበቀው ከባድ ዝናብ ለወቅቱ የእርሻ ስራ እንቅስቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረውም ጠቁሟል። ሆኖም ሊኖሩ የሚችሉ ተያያዥ ስጋቶችን ለመቀነስና የሚኖሩትን መልካም አጋጣሚዎች ለመጠቀም የቀረቡትን የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክረ ሀሳቦች በሁሉም ደረጃ በተገቢው ሁኔታ መተግበር እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል። በቀጣዮቹ ቀናት የሚኖረውን የአየር ሁኔታ የተመለከተው ትንበያ ለክረምት ዝናብ መፈጠር አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ከቀን ወደ ቀን እየተስፋፉና እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ ያሳያል ነው ያሉው። ከዚሁ ጋር በተያያዘም፣ በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የዝናብ መጠንና ሥርጭት እንደሚኖራቸው የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ ሲልም ገልጿል። በዚህም ርጥበታማው የአየር ሁኔታ በተለይም በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብና በመካከለኛዉ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ በመጠንም ሆነ በሥርጭት እየተስፋፋ ከመሄዱ ጋር ተያይዞ ብዙ ቦታዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል። ጥቂት ስፍራዎቸ ላይ ደግሞ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች አመላክተዋል ነው ያለው። በሚቀጥሉት ቀናቶች ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ላይ በመነሳት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ብዙ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ነው መረጃው ማመላከቱንም አስታውቋል። በተጨማሪም አልፎ አልፎ በውሃ አካላትና በካባቢ አየር ውስጥ ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽ ላይ በመነሳት በምዕራብ እና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች በ24 ሠዓት ውስጥ ከ30 ሚሜ በላይ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች አመላክተዋል ብሏል። በቀጣይ አስር ቀናት የክረምት ወቅት መጀመሩን ተከትሎ በአብዛኛው ርጥበት ተጠቃሚ በሆኑ ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ የሆነ የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው ይጠበቃል ሲልም ገልጿል። የሚኖረውን አዎንታዊ የርጥበት ሁኔታ በአግባቡ ለመጠቀምና አሉታዊ ሁኔታን ለመቀነስ የውሃ ማንጣፈፍያ እና የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀት እንደሚገባም ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።
ብርቅዬ የዱር እንስሳትና ዕጽዋትን ከህገ ወጥ አደንና ዝውውር የመጠበቅ ተግባርን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል - ሚኒስቴሩ
Jun 9, 2025 141
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2017(ኢዜአ)፦ በብሔራዊ ፓርኮች ውስጥ የሚገኙ ብርቅዬ የዱር እንስሳትና ዕጽዋትን ከህገ ወጥ አደንና ዝውውር የመጠበቅ ተግባርን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ገለጹ። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ሕገ-ወጥ የዱር እንስሳት ዝውውርን ለመቆጣጠር ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት አምስት ቀናት የሚቆይ የባለድርሻ አካላት ስልጠና በአዲስ አበባ አስጀምሯል። በስልጠናው የአየር መንገድ ተቆጣጣሪ አካላት፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ተወካዮች፣ ኢንተርፖል፣ የአቬዬሽንና ሌሎች ተቋማት ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ በዚሁ ወቅት፤ ስልጠናው ሕገ-ወጥ የዱር እንስሳትና ዕፅዋት ዝውውርን መቆጣጠር እንዲቻል ግንዛቤ በመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንደሚያበረክት ገልጸዋል። የፀጥታ እና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት የዱር እንስሳትና ዕፅዋትን ከህገ ወጥ አደንና ዝውውር የመጠበቅ ተግባርን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ጠይቀዋል። በዚህም ብሔራዊ የዱር እንስሳትና ዕፅዋት ጥበቃ ፓርኮችና የማህበረሰብ ጥብቅ የደን ስፍራዎች ለቱሪዝም ኢኮኖሚያዊ አቅም እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ብርቅዬ የዱር እንስሳት በሚገኙባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን በማሳተፍ የአትክልትና ፍራፍሬ እና ሀገር በቀል ዕፅዋት ልማትን ጨምሮ የኢኮ ቱሪዝም ጥበቃ ልማት ላይ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ፤ ስልጠናው ሕገ-ወጥ የዱር እንስሳት ዝውውርን ለመቆጣጠርና በትብብር ለመስራት ያለመ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ህገ-ወጥ የዱር እንስሳት ዝውውር ዓይነቱንና ቅርጹን እየቀያየረ እንደሚፈጸም ገልጸዋል። ስልጠናው ሕገ-ወጥ የዱር እንስሳት አደንና ዝውውር ወንጀሎችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላትን ሚና ለማሳደግ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረውም አስረድተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 100
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ።   በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 828
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል።   የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 554
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል።   ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1174
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 523
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች።   የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች።   ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ።   ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።      
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 676
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ቱሪዝሟ እያደገ የመጣው፣በባህላዊ ምግቦቿ እና ቡናዋ ዓለም አቀፍ እውቅና የተቸራት ኢትዮጵያ
May 11, 2025 514
በባህላዊ ታሪኳ እና ልዩ በሆኑ የምግብ አዘገጃጀቶች የምትታወቀው ኢትዮጵያ የበለጠ የዓለምን ትኩረት እየሳበች ትገኛለች። የናይጄሪያው ቢዝነስ ደይ ጋዜጣ ጋዜጠኛ ቺሶም ማይክል በጋዜጣው ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ብዙዎች በአፍሪካ ምርጡ ምግብ እና በዓለም ላይ ምርጡ ቡና ብለው የሚናገርላት ሀገር ብትሆንም አገሪቷ አሁንም ከሌሎች የአህጉሪቱ መዳረሻዎች ጋር ስትነጻጸር በአንፃራዊነት ጥቂት ቱሪስቶችን የምታስተናግድ ሀገር እንደሆነች ይገልጻል። ሞሮኮ እ.አ.አ በ2024 17 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቱሪስቶችን ስትቀበል ኬንያ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ጎብኚዎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያም የበርካታ ቱሪስቶች መዳረሻ የመሆን ጊዜዋ እየመጣ ይመስላል። የተባበሩት መንግስታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት (ዩኤንደብሊውቲኦ) በቅርቡ ባወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው እስከ 2024 ባለው አምስት ዓመት ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ አለም አቀፍ ቱሪስቶች በ40 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። 54ቱንም የአፍሪካ ሀገራት የጎበኙ አንድ ተጓዥ ኢትዮጵያን ሁለተኛ የቱሪዝም ተመራጭ አድርገውታል። "ለዚች ሀገር በጣም የተለየ ነገር ነው ያለኝ ብዙ ጥሩ የተፈጥሮ ቦታዎች አሏት" ብሏል። ይህም የኢትዮጵያ መንግስት ቱሪዝምን የኢኮኖሚያዊ እድገት ቁልፍ አካል ለማድረግ ያሳየው ቁርጠኝነት እንደሆነ ጋዜጠኛው ይገልጻል። በዩቲዩብ ላይ ከ5 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያለው የቱሪዝም ይዘት ላይ ድሪው ቢንስኪ ይህንኑ ሀሳብ ይጋራል። “ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ምርጥ ምግብ አላት። እንጀራ በጣም ጣፋጭ ነው በዓለም ሌላ ቦታ እንደዚህ ያለ ምግብ የለም። በአፍሪካ ምርጥ ምግብ፣ በዓለም ምርጥ ቡና ያለው እዚህ ሀገር ነው።” "እንጀራ ከጤፍ የተሰራ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ምግብ ውስጥ በጣም ዋና አካል ነው። እንጀራው ከብዙ ምግቦች እና ቅመሞች ጋር ይቀርባል።" ሲል ገልጿል። ኢትዮጵያዊያን የሚታወቁት በምግብ እና ቡና ብቻ አይደለም። ቱሪስቶች በኢትዮጵያ የተፈጥሮ እና ታሪካዊ መዳረሻዎች በጣም ይማረካሉ። በድንጋይ ከተቀረጹ የላሊበላ ውቅር አብያተ ቤተክርስቲያናት በጣም የሚጎበኙ የቱሪዝም መስህብ ነው። በጥልቅ ስምጥ ሸለቆ የታጀበው የሰሜን ተራሮች ለሰዎች ምቹ የእረፍት ጊዜ የሚሰጡ ናቸው። መዲናዋ አዲስ አበባ የባህል እና የምግብ ሁነቶች ማዕከል ናት። የኢትዮጵያ የቱሪዝም ልማት አካሄድ ቅርስ፣ መልክዐ ምድሮች እና ባህላዊ ልምዶችን ጨምሮ የተለያዩ መዳረሻዎችን ማስተዋወቅ ላይ ያተኮረ ነው። ካላት የቱሪዝም መዳረሻ አንጻር በኢትዮጵያ ብዙ ጎብኚዎች ባይኖሩም ያሏትን እድሎች በማስተዋወቅ ተደራሽነቷን እያሰፋች ነው። ልዩ ማንነት ያለው እና ጥልቅ ታሪክ ያላትን ኢትዮጵያን መጎብኘት ለሚሹ ሰፊ የቱሪዝም እድሎችን የምታቀርብ ሀገር ናት ይላል ጋዜጠኛው። በኢትዮጵያ ቱሪዝም እየጨመረ ብዙ ጎብኚዎች በምግቧ፣ ቡናዋ እና ታሪካዊ መዳረሻዎቿ እየተሳቡ ነው። በኢትዮጵያ ባህል እና የምግብ አሰራር ከዕለት ተዕለት የዜጎች ህይወት የተቆራኘባት ሀገር ናት። ኢትዮጵያ የተለየ ነገር ማቅረቧን ቀጥላለች። የቱሪዝም ሀብቶቿ ገና ያልተነካ ነው ኢትዮጵያ የወደፊት የዘርፉ እድገት አቅም ትልቅ ነው በማለት ጋዜጠኛ ቺሶም ጽሁፉን ቋጭቷል።  
የግማሽ ምዕተ ዓመቱ ታሪካዊ ጉብኝት፡-
Apr 16, 2025 1287
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቬይትናም ጉዞ በአውሮፓዊያኑ አቆጣጠር ነሃሴ 2018 የቬይትናም የቀድሞ ፕሬዝዳንት ትራን ዳይ ኳንግ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ የመጀመሪያው የቬይትናም መሪ ናቸው። የፕሬዝዳንቱ የሶስት ቀናት ጉብኝት ትኩረት በኢትዮጵያ እና ቬይትናም መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ፤ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነበር። ኳንግ በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ጋር የሁለትዮሽ ውይይቶችን አድርገዋል። ከፕሬዝዳንቱ ጋር ወደ ኢትዮጵያ የመጣው የቬይትናም የልዑካን ቡድን የቢዝነስ ማህበረሰብ አባላት ከግሉ ዘርፍ የቢዝነስ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት ያደረገ ሲሆን ምክክሩ በሀገራቱ የንግድ ተወካዮች መካከል ቋሚ ትስስርን መፍጠር ያለመ ነው። የአገራቱን ረዥም ዕድሜ ያስቆጠረ ታሪካዊ ግንኙነት መሰረት በማድረግ የሁለትዮሽ እና የባለብዝሃ ወገን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል በወቅቱ። ኢትዮጵያ እና ቬይትናም በምጣኔ ሀብት፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ በፓርላማ ለፓርላማ፣ እና በመሳሰሉት የልማት መስኮች በትብብር ለመስራት ከዚህ በፊት የፈረሟቸውን ስምምነቶች ሥራ ላይ ለማዋል እንደሚገባም ተስማምተው ነበር። ትራን ዳይ ኳንግ ኢትዮጵያን ከጎበኙ ሰባት ዓመታት አለፉ። ከሰባት ዓመታት በኋላ በኢትዮጵያ እና ቬይትናም የሁለትዮሽ ትብብር ታሪክ ኢትዮጵያዊ መሪ የደቡብ ምስራቅ ኤስያዊቷን ሀገር መሬት ለመጀመሪያ ጊዜ ረገጠ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ቬይትናም ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር) ቬይትናምን የጎበኙ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ መሪ ናቸው። ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል የሁለትዮሽ ትብብር ዑደት ውስጥ ትልቅ ትርጉም እና አንድምታ ያለው ነው። ኢትዮጵያ እና ቬይትናም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1976 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ትብብር እ.አ.አ በ2026 50ኛ ዓመቱን ይደፍናል። በነዚህ ዓመታት ውስጥ በቬይትናም በመሪ ደረጃ የጎበኘ የኢትዮጵያ መሪ የለም። ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቬይትናምን መጎብኘታቸው በሁለቱ ሀገራት ትብብር የሚነሱ ታሪካዊ መሪ ያደርጋቸዋል። ቬይትናም ኒውስ፣ ቮይ ኦፍ ቬይትናም፣ ናን ዳን ኦንላይን እና ቬይትናም ፕላስ የተለያዩ የሀገሪቷ መገናኛ ብዙሃን ታሪካዊው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ትብብር ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ዘግበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቬይትናም በሚኖራቸው ቆይታ በ2025 የፒ4ጂ ቬይትናም ጉባኤ ላይ እንደተሳተፉ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በቆይታቸው ከቬይትናም የፀሃይ ኃይል ማመንጫዎች በማምረት ወደ ውጭ የሚልከውን ቶዮ ሶላር የተባለውን ፋብሪካ ጎብኝተዋል።   ድርጅቱ በቅርቡ በሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ በመግባት በኢትዮጵያ ሥራ ጀምሯል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድርጅቱ ከፀሃይ ኃይል ማመንጫ ምርት ባሻገር የኃይል ማመንጫ ፋብሪካ እንዲያቋቁም አበረታተዋል። ይኽም ሀገራችን ከያዘችው የአረንጓዴ አሻራ ፖሊሲ ጋር የተናበበ በማደግ ላይ ላለው የኃይል ጥያቄም ምላሽ በመስጠት ሊያግዝ የሚችል መሆኑን መግለጻቸውን የጽህፈት ቤቱ መረጃ ያመለክታል። የቬይትናም መገናኛ ብዙሃን ጉብኝቱ የሀገራቱን የሁለትዮሽ እና የባለብዝሃ ወገን ትብብር እንደሚያጠናክር በመግለጽ ላይ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ቬይትናም ባለፉት ጥቂት ዓመታት የሁለትዮሽ ትብብራቸውን የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችላቸውን ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተደረገው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ቬይትናም የጋራ የፖለቲካ ምክክር የዚሁ ፍላጎት ማሳያ ነው። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ታሪካዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ እና ቬይትናም ግንኙነት የላቀ ትብብር እና ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ ከፋች ነው።   ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው አካል የሆነ ውይይት ከቬይትናም ኮሚኒስት ፓርቲ ዋና ፀሃፊ ጋር በፓርቲው ማዕከላዊ ጽሕፈት ቤት አካሂደዋል። በውይይታቸውም በተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ጉዳዮች ብሎም በሀገራዊ ልማት እና አስተዳደር ጉዳዮች መክረዋል። የቬይትናም ጠቅላይ ሚኒስትር ፋም ሚን ቺን በቤተ መንግሥታቸው ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋዊ የአቀባበል ስነ-ስርዓት አድርገውላቸዋል። ሁለቱ መሪዎችና የልኡካን ቡድኖቻቸው የሁለትዮሽ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፥ በሁለቱ ሀገራት የተካሄዱ ማሻሻያዎችን እንዲሁም ለትብበር የሚሆኑ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በተለይም የልምድ ልውውጥንና ኢንቨስትመንትን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ተለዋውጠዋል።   መሪዎቹ የትብብር ሰነዶችን የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይም የተገኙ ሲሆን፥ በንግድ እና በትምህርት ትብብር ላይ የመግባቢያ ስምምነቶች ተፈርመዋል። በተጨማሪም በአዲስ አበባ እና በሃኖይ መካከል በኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀጥታ በረራ መንገድ የሚያመቻች የሲቪል አቪዬሽን ስምምነት ተደርጓል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የቬይትናም ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከተመሰረተ ከሃምሳ አመታት በኋላ የመንግስት መሪ ያደረጉት የመጀመሪያ ይፋዊ የኦፊሴላዊ ጉብኝት ነው።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ2025 የፒ4ጂ ቬይትናም ጉባኤ ላይ ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “ዘላቂ እና ሕዝብን ማዕከል ያደረገ አረንጓዴ ሽግግር” በሚል ጭብጥ እየተካሄደ ባለው የ2025 ፒ4ጂ ቬይትናም ጉባኤ የአየር ንብረት ጥበቃን ለማራመድ አስፈላጊ የሆኑ ሶስት ቁልፍ የተግባር ነጥቦችን አፅንዖት ሰጥቼ አንስቻለሁ ብለዋል። በዚህም አንደኛ የአየር ንብረት ጥበቃ የገንዘብ አቅርቦትን የቅድሚያ ቅድሚያ በመስጠት በቂ፣ ተገማች እና ዘላቂ በሆኑ ምንጮች ማረጋገጥ ይኖርብናል ሲሉም ገልጸዋል። ሁለተኛ ዘላቂ ልማትን ለመደገፍ እና የአኅጉሩን ወሳኝ ሥነምኅዳር ጥበቃ ለማድረግ በአለም የኃይል ምንጭ ኢንቬስትመንት ሽፋን ውስጥ የአፍሪካን ድርሻ በአሁኑ ወቅት ካለበት ሁለት ከመቶ በ2030 ወደ ሃያ ከመቶ ማሳደግ ይገባናል ነው ያሉት። ሶስተኛ የብዝኀ ሕይወት ጥፋትን እና የምድር መራቆትን በመዋጋት ተፈጥሮን ለመጠበቅ አፋጣኝ ርምጃዎች ሊወሰዱ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል። ይኽም እንደ አረንጓዴ አሻራ ያሉ ሕዝባዊ ሥራዎችን በገንዘብ መደገፍን በዚህም ለየአካባቢው ኅብረተሰብ ከአድልዎ የፀዳና ፍትኀዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥን ያካትታል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የቬይትናም ጠቅላይ ሚኒስተር ፋም ሚን ቺን በይፋዊ ጉብኝታችን ወቅት ላደረጉት የደመቀ አቀባበል እና የክብር መስተንግዶ አመሰግነዋል። “ኢትዮጵያና ቬይትናም የሚያመሳስሏቸው ብዙ የጋራ ጉዳዮች አሏቸው። ሁለታችንም ትልቅ እና ለሥራ የተነሳሳ ወጣት ሕዝብ ያለን፣ ለልማት እና እድገት የቆረጥን እንዲሁም በታሪካችን ሂደትም በፅናታችን የምንታወቅ ሀገራት ነን። ውይይታችን በንቁ ተሳትፎ የሚገለጥ እና ጥልቀትም የነበረው ነበር። ለጋራ እድገት እና ትብብር ያለንን ፅኑ የጋራ ተነሳሽነትም አንፀባርቀናል። የሃሳብ ልውውጣችን በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ለጠንካራ ፖለቲካዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር በር ከፍቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ፋም ሚን ቺን በቅርብ ኢትዮጵያን በሚጎበኙበት ወቅት የጋራ ርዕዮቻችንን የበለጠ የምናጠናክርበት እና በዛሬው የአለማችን አውድ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን ይበልጥ የምናፀናበት ይሆናል” ሲሉ አረጋግጠዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሃኖይ እየተገነባ የሚገኘውን ትልቅ የዘመነ ከተማ (የስማርት ሲቲ) ፕሮጀክት ጎብኝተዋል። ይኽም ለኢትዮጵያ የከተማ ልማት ሥራ የሚሆን ተሞክሮ የመቅሰም ተግባር አካል መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጉብኝቱ ዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር በመላው ኢትዮጵያ እየተካሄዱ ያሉ የዘመናዊ ከተማ ፕሮጀክቶችን ለማላቅ የሚደረግ ፍላጎትና ጥረትን እንደሚያሳይ ገልጿል። ከቬይትናም ፕሬዝዳንት ጄነራል ሉዎንግ ኩዎንግ ጋር ውይይት አድርገዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ ከብሔራዊ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ትራን ታንህ ማን ጋርም መክረዋል። ውይይቶቹ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቬይትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ የሚያደርጉትን ይፋዊ ጉብኝት አካል መሆኑን ነው። በሁለቱም ውይይቶች ስለ ሀገረ መንግሥት ቀጣይነት፣ የፖለቲካ ትብብር፣ የለውጥ ጥረቶች የተነሱ ሲሆን በብዙ ዘርፎች የሁለትዮሽ ትስስሮችን እና ትብብሮችን ይበልጥ ለማጠናከር የሚቻልባቸው መንገዶች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 2638
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 2278
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 2496
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 3630
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 1980
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 1976
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3382
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 47359
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 42763
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 27629
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 24961
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 23226
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 21450
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 21219
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 20848
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 47359
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 42763
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 27629
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 24961
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ቢልጌትስ ታላቁን የኢትዮጵያ የክብር ኒሻን እንዴት ተቀዳጁ?
Jun 2, 2025 313
በሀገረ አሜሪካ ሲያትል ውስጥ ተወልደው ያደጉት ቢል ጌትስ የዕውቁ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ማይክሮ ሶፍት መስራችና ባለቤት ናቸው። ከግማሽ ምዕተ ዓመት በፊት ከአጋራቸው ፖል አለን ጋር የመሰረቱት ማይክሮሶፍት ቢልጌትስን ከምድራችን ግንባር ቀደም ቱጃሮች አንዱ አድርጓቸዋል። ቢልጌትስ ከኮምፒዩተር ቴክኖሎጂው ማይክሮሶፍት ባሻገር በፈረንጆቹ 1990 በቀድሞ ስሙ ‘ቢል ኤንድ ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሸን’ በአሁኑ መጠሪያው ‘ጌትስ ፋውንዴሽን’ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት አቋቁመዋል። ፋውንዴሽኑ የሰው ልጆች ሁሉ ዕኩል ዕድልና የተሻለ ነገ ይኖራቸው ዘንድ በተለይም በግብርና እና በጤናው ዘርፍ መልከ ብዙ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ በተለያዩ ክፍላተ ዓለማት ተግብሯል። የጌትስ ፋውንዴሸን ተልዕኮ “ሁሉም ሰው ጤናማና ምርታማ ሕይወት የሚመራባት ምቹ ዓለም መፍጠር” የሚል ነው። የጌትስ ፋውንዴሽን በስፋት ድጋፍ ካደረገባቸው ሀገራት መካከል ታዲያ ኢትዮጵያ አንዷ ናት። ፋውንዴሽኑ በኢትዮጵያ በአውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ2000 ስራ የጀመረ ሲሆን እ.አ.አ በ2012 ቢሮውን በአዲስ አበባ በመክፈት ከኢትዮጵያ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና ለጋሾች ጋር በትብብር እየሰራ ይገኛል።   ኢትዮጵያውያን ጤናማ ህይወት እንዲኖራቸውና የኑሮ ዘይቤያቸው እንዲሻሻል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን መደገፍ የፋውንዴሽኑ ግብ ነው። ከለጋሾች በተገኘ ድጋፍ የዜጎችን ህይወት ማሻሻል ላይ ከፍተኛ ለውጦች መታየታቸውንና በእናቶችና ህጻናት ጤና፣ ትምህርት እና ግብርና ምርታማነት አመርቂ ስኬቶች መመዝገባቸውን ያመለክታል። ፋውንዴሽኑ ጥረቶቹን ከኢትዮጵያ መንግስት የትኩረት አቅጣጫዎች ጋር በማሰናሰን በስርዓተ ጾታ እኩልነት፣ በቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ተጠቃሚነት፣ በፋይናንስ አካታችነት እና በንጽህና አጠባበቅና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ እየሰራ ይገኛል። ለዚህ ተግባሩም በኢትዮጵያ ከ777 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል። ከጌትስ ፋውንዴሽን ስራዎች መካከል በጤናው ዘርፍ የጤና ኤክስቴሽን ፕሮግራም አማካኝነት በገጠራማ አካባቢዎች ዜጎች መሰረታዊ የጤና አገልግሎትን እንዲያገኙ ማስቻል ይጠቀሳል። የኤችአይቪ/ኤድስ፣ የሳምባ ምች እና ወባ በሽታዎችን በምርምር፣ በገንዘብ ድጋፍ እና ከአጋር አካላት ጋር በመሆን ለመከላከል እየሰራ ነው። በግብርና ዘርፍ ደግሞ የግብርና ምርታማነትን የማሳደግ አላማ ላነገበው የስንዴ ክላስተር እርሻ ኢኒሼቲቭ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን አምራቾች ከቤት ፍጆታነት ወደ ገበያ የሚተርፍ ምርት እንዲያገኙ ደግፏል። አነስተኛ ይዞታ ላላቸው አርሶ አደሮች የዶሮ ጫጩቶችን ለሚያቀርበው የግል ኩባንያ ኢትዮ ቺክን ድጋፉን ለግሷል። የፋውንዴሽኑ መስራችና ሊቀመንበር ቢል ጌትስ ባሳለፍነው መስከረም በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የክላስተር የስንዴ ማሳዎችንና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ስራዎችን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር መጎብኘታቸው ይታወሳል። ቢል ጌትስ ከጉብኝቱ በኋላ ባሳተሙት መጣጥፍ በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው በግብርናው ዘርፍ የመጣው እመርታ እንዳስደነቃቸው አስፍረዋል።በኢትዮጵያ ያልታረሱ ማሳዎችን በማረስ፣ በግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቅምና ሌሎች የሪፎርም ስራዎችን በመተግበር በቅርብ ዓመታት ተምሳሌታዊ የሆነ ምርትና ምርታማነት መመዝገቡን ገልጸው ነበር።   በዚህም ፋውንዴሽኑ ባለፉት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያን ግብርና ዘርፍ በመደገፉ ትልቅ ኩራት ይሰማዋል ብለው ነበር ቢል ጌትስ ። ጌትስ ፋውንዴሽን በሌሎች የልማት ኢኒሼቲቮች ለአብነትም የኢትዮጵያ መንግስት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ፣ በፋይናንስ አካታችነት፤ በመረጃ አሰባሰብ፣ ምርምር እና ፖሊሲ ትግበራ የሀገር በቀል አቅሞችን የመገንባት ስራዎችን ይደግፋል። ኢትዮጵያም ጌትስ ፋውንዴሽን በተለያዩ መስኮች ላለፉት 25 ዓመታት ላከናወናቸው ስራዎች እውቅና ሰጥታለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያን ታላቁን የክብር ኒሻን ለቢል ጌትስ ትናንት ማምሻውን በብሔራዊ ቤተመንግሥት በተካሄደ ሥነ-ሥርዓት ሸልመዋል። ይህ የከበረ ሽልማት የጌትስ ፋውንዴሽን በኢትዮጵያ ላበረከታቸው አሻጋሪ ሥራዎች እና ታላላቅ ዘመን ተሻጋሪ በጎ ተፅዕኖዎችን ያከበረ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በንግግራቸው ለቢል ጌትስ ፋውንዴሽን የ25 ዓመታት አሸጋጋሪ ሥራዎች ምስጋና አቅርበዋል። ቢል ጌትስ ከቴክኖሎጂ ፈር ቀዳጅነት ወደ በጎ አድራጊነት ያደረጉትን ጉዞ በማውሳትም ዝቅ ብሎ በማገልገል፣ በአክብሮት እና በእኩልነት እምነት ላይ የተመሠረተውን አገልግሎታቸውን አድንቀዋል። ፋውንዴሽኑ በጤና፣ በግብርና፣ በዲጂታል መታወቂያ የሚያደርገው ብርቱ ድጋፍ ብሎም በመከባበር ላይ የተመሠረተ የፋውንዴሽኑ የትብብር ጉዞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተወስቷል። ቢል ጌትስ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ለዘለቀ ጊዜ የሰዎችን ጤናና ምርታማነት ለማሻሻል በፋውንዴሽናቸው አማካኝነት ላደረጉት በጎ ድጋፍ ኢትዮጵያ የክብር ኒሻን ሸልማቸዋለች።  
ደመና ማበልጸግ በኢትዮጵያ የአራት ዓመት ጉዞና ስኬት
Apr 25, 2025 1565
ደመና ማበልጸግ(Cloud Seeding) ምንድን ነዉ? የደመና ማበልጸግ በደመና ውስጥ ያለውን የዝናብ መጠን ወይም ዓይነት የሚለውጥ(የሚጨምር) የአየር ሁኔታ መቀየሪያ ዘዴ ነው። ይህም ማለት በመሰረታዊነት ዝናብ ሊሆን የሚችልን ነገር ግን አቅም ያጣን ደመና ወደ ዝናብ እንዲቀየር በማፋጠን መዝነብን የመጨመር ተግባር ነው። የደመና ማበልጸግና ማዝነብ ቴክኖሎጂ በ1940ዎቹ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ። ደመና ማበልጸግ ቴክኖሎጂን ለመተግበር የተለያዩ መንገዶች ቢኖሩም በዋናነት በአውሮፕላን፣ ባሎን፣ ሮኬት፣ ድሮን እና መሬት ላይ በሚቀመጥ ጀነሬተር በመታገዝ ደመና ላይ ጨው መሰል ብናኝ በመርጨት በዝናብነት ወደ ምድር የማይወርድ ደመናን አቅም ኖሮት እንዲዘንብ ወይም እንዲወርድ ማድረግ ነው። ይህ ሂደት ሰው ሰራሽ ሲሆን የደመና መዝነብን አቅም ከ15-30 በመቶ በማሳደግ ዝናብ እንዲከሰት የማድረግ አቅም አለው። ይህ ቴክኖሎጂ በተለያዩ ሀገራትና ጊዜያት ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን በ2013 ዓ.ም ሀገራችን ከተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ጋር ባላት ጠንካራ ግንኙነትና ትብብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ችሏል።   በወቅቱም ከተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ብሔራዊ ሜትሮሎጂ ማዕከል በመጣ አውሮፕላንና የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የአየር ላይ ኦፕሬሽን ተደርጓል፤ የማቴሬሪያልና የሙያ ድጋፍ ተገኝቷል።ድርቅ አጋጥሞ በነበረበት በቦረና ጉጂ አካባቢ የዝናብ ማዝነብ ኦፕሬሽን ተከናውኗል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚሰጠው አቅጣጫ ኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የተለያዩ ተቋማትን አስተባብሮ ሀገራችን የቴክኖሎጂው ባለቤት የምትሆንበትን መሰረተ ልማትና ሲስተም እንዲያበለጽግ ኃላፊነት ተሰጥቶታል። ሲስተሙን ከመጠቀም አልፎ ከዚህ ቀደም በቻይና ተመርቶ ስንጠቀምበት የነበረው የደመና ማበልጸጊያ(ማዝነቢያ) ግራውንድ ጀነሬተር በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አስተባባሪነት በሀገራችን በሙሉ አቅም መሥራት ተችሏል።   በራስ አቅም ልንሰራው በመቻላችን የቴክኖሎጂ ባለቤትነታችንን ከማረጋገጥ ባሻገር የውጭ ምንዛሪን በማዳን ከፍተኛ አገራዊ ጥቅም ሊገኝበት ችሏል። በ2015 ዓ.ም የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ ውሎ በሀገራችን በዝናብ እጥረት የሚያጋጥመውን አደጋ ለመከላከል ለዝናብ ማዝነቢያ የግራውንድ ጄኔሬተር ማምረቻ የሚሆን የፕሮጀክት በጀት መድቧል። የፕሮጀክት በጀቱንም የማምረት ሥራው ሂደትና ስኬት እየታየ በሁለት ዙር ለመልቀቅ ከኢፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር ውል በተፈራረመው መሰረት በመጀመሪያው ዙር 20 ግራውንድ ጀነሬተር ማምረት ሥራ በስኬት በማጠናቀቅ በኦሮሚያ ክልል በሚፈለግበት ወረዳዎች በሟቋቋም ወደ ኦፕሬሽን እንዲገቡ ተደርገዋል። በሁለተኛው ዙር 25 የግራውንድ ጀነሬተሮቹን የማምረት ሥራው ተጠናቋል፡ ወደ ኦፕሬሽን እንዲገቡም ተደርገዋል። በአጠቃላይ 45 ጄኔሬተሮች በማምረት የዝናብ እጥረት ለሚያጋጥማቸው ቦታዎች (ደቡብና ምሥራቅ ኦሮሚያ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንሶና ደቡብ ኦሞ ዞን፣ በሶማሊ ክልል፣በእንጦጦ ተራራ) ተተክሏል። የአየር ንብረት እና ክላውድ ሲዲንግ መሰረታዊ እውቀት፣የሲስተም ተከላና ኦፕሬሽን በመስክና በታቀደ ስልጠና አቅም ተገንብቷል። ድሮንን በመጠቀም ሙከራዎች ተደርገዋል። በሚቀጥሉት ጊዜያት በአየር ላይም ኦፕሬሽን ስናደርግ ቴክኖሎጂን በራስ አቅም፣ ባለሙያና ቴክኖሎጂ ለመስራት ጥናትና ትግበራው የሚቀጥል ይሆናል። በአገር ደረጃ የሚመለከታቸውን ተቋማት በማሳተፍ የቴክኖሎጂ ባለቤትነትና ተጠቃሚነታችንን የሚያረጋግጥ ተጨማሪ ምርምርና ከፍ ያለ ሥራ ይሰራል። የደመና ማበልጸግ በኢትዮጵያ ፕሮጀክት በዋናነት በኦፕሬሽናልና በተግባራዊ ምርምር ቴክኖሎጂን የመጠቀም፣አስቻይ መሰረተ ልማት የማቋቋም፣ የደመና ማበልጸግ ቴክኖሎጂ ልማትን በሚያሳልጡ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ ተልዕኮውን የሚፈጽም ነው።   ይህ ፕሮጀክት ወደ ስራ ሲገባ የተለያዩ ዓላማዎችን አንግቦ ሲሆን የመጀመሪያው በሀገራችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ከባለድርሻ አካል ጋር በመሆን እገዛ ማድረግ፤ በምርምር ፣ ልማት እና ትግበራ ላይ የተመሰረተ ዳመናን ማልማት የሚያስችል የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲኖር ማስቻል ፣በዘርፉ ልህቀት ማዕከል ማቋቋም ነው። ከዚህ በተጨማሪ የዳመናን ማልማት ምርምር፣ ልማት እና ትግበራን ለማሳለጥ የሚያግዙ ሀገራዊ የፖሊሲና የመሠረተ-ልማት ማዕቀፎችን ማዘጋጀት ማቅረብ፤ እንዲሁም በዳመና ልማት ዙሪያ የሚሰማሩ ባለድርሻ አካላት እና የተቋማት ትስስርን ምቹ ምህዳር መፍጠር ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም