አርእስተ ዜና
ጉባኤው ወጣቶች የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ አፍሪካን በመገንባት ሂደት ሚናቸውን ይበልጥ እንዲያጎለብቱ የሚያግዝ ነው -ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር)
Mar 27, 2025 10
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦የፓን አፍሪካ ወጣቶች አመራር ጉባኤ ወጣቶች የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ አፍሪካን በመገንባት ሂደት ሚናቸውን ይበልጥ እንዲወጡ እንደሚያስችል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የፓን አፍሪካ ወጣቶች አመራር ጉባኤ ከመጋቢት 25 እስከ 27/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድም ተገልጿል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ አፍሪካ ከህዝቧ አብዛኛው ወጣት መሆኑን ያነሱ ሲሆን ፥ በጠንካራ ማህበራዊ እሴቶች፣ጥበባትና በተፈጥሮ ጸጋዎች የታደለች አህጉር ናት ብለዋል። ጉባኤው “የወጣቶችን አቅም ለበለፀገች አፍሪካ” በሚል መሪ ሃሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል ብለዋል። በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው ይህ አህጉራዊ ጉባኤ ዋና አላማ ወጣቶች የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ አፍሪካን በመገንባት ሂደት ውስጥ የመሪነት ሚናቸውን እንዲያበረክቱ ለማስቻል መሆኑን ጠቁመዋል። የአፍሪካ ወጣቶች ቻርተር ላይ የተደነገጉ መብቶችና ግዴታዎችን ለማስገንዘብም ጉባኤው ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል። የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤን ለወጣቱ ለማስረጽና በአፍሪካ ህብረት መሪዎች ጉባዔ የተያዘው አህጉራዊ መሻቶችን በጋራ እውን ለማድረግ ነው ብለዋል። የወጣቶችን ዲፕሎማሲ አቅም በማሳደግ ወጣቱ ከሀገሩ አልፎ በአህጉርና በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የአፍሪካን መብትና ጥቅም ማስከበር እንዲችል ጉባዔው ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል ፡፡ መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የወጣቱን ጉዳይ የዕቅዳቸው አካል አድርገው በመስራት ረገድ ለመወያየት ምቹ አጋጣሚ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት የነጻነትና የለውጥ ምሳሌ ናት ያሉት ሚኒስትሯ፥ ለአፍሪካ አንድነትና ትስስር መጠናከር ከፍተኛ ሚና እያበረከተች ያለች ሀገር መሆኗን አንስተዋል። የፓን አፍሪካን እሳቤ በመላው አፍሪካ እንዲጎለብት የወጣቱ ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በርካታ ተግባራትን በማከናወን ውጤቶች እየተመዘገቡበት የሚገኘው የመደመር እሳቤ ለፓን አፍሪካኒዝም መጎልበት በሚኖሩ እሴቶች ላይ የፓናል ውይይት እንደሚደረግም ገልጸዋል። ከዚህ ባለፈም የኢትዮጵያ ታሪክና እሴት የሚተዋወቅበትና በመዲናዋ የተሰሩ ልማቶች የሚጎበኙበት እንዲሁም የባህል ልውውጥ የሚደረግበት ፕሮግራም እንደሚኖርም ጠቁመዋል። በመድረኩ ከ53 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ አንድ ሺህ የሚሆኑ ወጣት መሪዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች፣የተለያዩ መንግስት ስራ ኃላፊዎች፣ የወጣት አደረጃጀቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንደሚሳተፉ አንስተዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ የዕውቀት፣ የሥነ-ጥበብና የኪነ-ጥበብ ቤት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Mar 27, 2025 15
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ የዕውቀት፣ የሥነ-ጥበብና የኪነ-ጥበብ ቤት ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ። ፕሬዝዳንቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ-ጥበብ እና ያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤቶችን ጎብኝተዋል።   ጉብኝታቸውም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤቶች ለዘርፉ ዕድገት እያበረከቱት ያለውን ሚና እና የስራ እንቅስቃሴያቸው ላይ ምልከታ ማድረግን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤት በአፍሪካ ደረጃ ከሚገኙ የሥነ-ጥበብ ተቋማት አንፃር ከፍ ያለ ዕውቀት የሚንሸራሸርበት ተቋም መሆኑን እንደተመለከቱ ተናግረዋል። በትምህርት ቤቱ ለሥነ-ጥበብ ስራ እና ለመማር ማስተማር ምቹ መደላድል የሚፈጥር የከባቢ ልማት እና ዘመናዊ ተቋም እየተገነባ እንደሚገኝም አንስተዋል። ለረጅም ጊዜ ተጠብቀው የቆዩ የትምህርት ቤቱ የአዕምሮ ውጤቶች አስገራሚ ናቸው ያሉት ፕሬዝዳንት ታዬ፤ ለዚህም ለዩኒቨርሲቲው አመራር፣ መምህራንና ተማሪዎች ምስጋና አቅርበዋል። የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤትም ለኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዕድገት የራሱን ጉልህ አሻራ ያሳረፈ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሙዚቃ ስራ ያለን ዋጋ ከፍ ያለ ነው ያሉት ፕሬዝዳንት ታዬ፤ ይህም ለኪነ-ጥብብ ዕድገት አበክረው የሰሩ ኢትዮጵያውያን የልፋት ውጤት መሆኑን አስገንዝበዋል።   በኢትዮጵያ የሙዚቃታሪክ ውስጥ ከድምጻውያን ባሻገር የመሳሪያ ተጫዋችና ተወዛዋዦች ተገቢውን ክብርና ዕውቅና ማግኘት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፥ ዩኒቨርሲቲው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መርሃ ግብሮች በማቀናጀት በኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ዘርፍም ሚናውን እየተወጣ ነው ብለዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በዩኒቨርሲቲው የኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤቶች ያደረጉት ጉብኝትም ስኬቶችን ለማስቀጠልና ጉድለቶችን ለማስተካከል ስንቅ መሆኑን አስረድተዋል። የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ-ጥበብና የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤቶች ለበርካታ ዓመታት በኢትዮጵያና የዓለም የሥነ-ጥበብና የኪነ-ጥበብ ሥራዎች ላይ ተጠቃሽ የሆኑ በርካታ የጥበብ ሰዎችን እያፈሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
Mar 27, 2025 16
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ ተፈራርመዋል። ስምምነቱ ኢንቨስትመንትን ለማነቃቃት የሚያስችል የሚዲያ አጋርነት እና የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ገጽታ ለማጠናከር ያለመ እንደሆነም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፥ ኮሚሽኑ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሽግግር በመምራት ሂደት ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የሀገሪቱን የኢንቨስትመንት እድሎች ማስተዋወቅ ቀዳሚ ስራው መሆኑን ተናግረዋል።   መንግስት ለኢንቨስትመንት ምቹ ምህዳር በመፍጠር በርካታ ተግባራትን ማከናወኑንም አስረድተዋል። እንዲሁም በተለያዩ ዘርፎች ወደ ሥራ የገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን የመደገፍ እና የመከታተል ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። እነዚህን ተግባራት በአግባቡ ለማስተዋወቅ የሚዲያ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፥ ስምምነቱ እምቅ አቅሞችን ለመጠቀም የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የኢንቨስትመንት መረጃዎችን በሙያዊ እውቀትና በጥራት ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም መሆኑን አንስተው ከአገልግሎቱ ጋር በመስራታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው ስምምነቱ የኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻነት ለማስፋት እንደ ትልቅ እድል የሚወሰድ ነው ብለዋል። አገልግሎቱ የኮሚሽኑ ህልሞች እውን እንዲሆኑ በዜናና ዜና ነክ የዘገባ ስራዎች የማስተዋወቅ ሚናውን እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ለዚህም የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድሎች፣ የተፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎችን እና እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ተደራሽ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
የመተባበርና የመተጋገዝ እሴትን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት በጋራ መስራት ይገባል
Mar 27, 2025 18
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦የመተባበርና የመተጋገዝ እሴትን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት በጋራ ልንሰራ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ተናገሩ። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሞሮኮ ንጉስ መሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑላሞች ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ለአንድ ሺህ አቅመ ደካሞች ማዕድ አጋርቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፥በኢትዮጵያ የሞሮኮ አምባሳደር ኔዛ አሎዩ ምሃምዲ እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ እንዳሉት፥ የመተባበርና የመተጋገዝ እሴትን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት በጋራ መስራት ይገባል። በረመዳን ጾም ለአቅመ ደካሞች የሚደረገውን የድጋፍ ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ነው የገለጹት። የሞሮኮ ንጉስ መሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑላሞች ፋውንዴሽን ላደረገው ድጋፍ አመስግነው፥ ሁላችንም ባለን አቅም መደጋገፍ አለብን ሲሉ አሳስበዋል። ምክር ቤቱ ተቋማትን በማስተባበር በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ስደተኞችን ጨምሮ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የኢፍጣር መርሃ ግብር ሲያካሂድ መቆየቱን ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ የሞሮኮ አምባሳደር ኔዛ አሎዩ ምሃምዲ በበኩላቸው፥ ፋውንዴሽኑ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉ ለኢትዮጵያ ያለንን ቅርበትና ወዳጅነት የሚያሳይ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ፋውንዴሽኑ ከተቋቋመ አንስቶ በተለያዩ አገራት ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች እያገዘ እንደሚገኝ በመጠቆም ዛሬ የተደረገው ድጋፍ ሞሮኮ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ወዳጅነትና ትብብር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይ ሞሮኮ በማህበራዊ እና ሰብዓዊ ትብብሮች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ወዳጅነት አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል። እገዛውን ያገኙ ወገኖች ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው የረመዳን ወር ሁሉም ለሰላም የሚተጋበትና ባለው አቅም የተቸገሩትን የሚረዳበት ነው ብለዋል።
ባንኩ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ የፋይናንስ አገልግሎቶች ማቅረቡን ያጠናክራል- አቤ ሳኖ
Mar 27, 2025 38
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የባንኩ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከማስተር ካርድ ጋር በመተባበር ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ ዓለም አቀፍ የዲጂታል ክፍያዎችን ማድረስ የሚያስችሉ ፕላስቲክ እና ቨርቹዋል ቅድመ ክፍያ ማስተር ካርዶችን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ ባንኩ የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት በዲጂታል ፋይናንስ ላይ ትኩረት ያደረጉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከዚህም መካከል አዳዲስ አስተማማኝ የፋይናንስ ዲጂታል ቅድመ ክፍያ አገልግሎቶችን ለደንበኞቹ ለማቅረብ እያከናወነ የሚገኘውን ተግባራትን አንስተዋል፡፡ ባንኩ ዛሬ ይፋ ያደረገው ዓለም አቀፍ ፕላስቲክ እና ቨርቹዋል ቅድመ ክፍያ ካርዶች አዳዲስ እና አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለደንበኞች ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል፡፡ ዲጂታል የቅድመ ክፍያ ካርዶች በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ነጋዴዎች ተቀባይነት ያላቸው መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፥ ክፍያ ካርዶች የባንኩን የላቀ የደህንነት እርምጃዎች የሚያሳዩ መሆኑንም ተናግረዋል። በቀጣይ ባንኩ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት ለመመለስ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ የዓለም አቀፍ ዲጂታል ክፍያዎችን ተደራሽ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የማስተር አፍሪካ ፕሬዝዳንት ማርክ ኤሊዮት በበኩላቸው፤ በንግድ ባንክ ይፋ የተደረገውን የቅድመ ክፍያ ዲጂታል ማስተር ካርድ በታዳጊ የአፍሪካ ገበያዎች ለማሳደግ ለያዘው ስትራቴጂ ቁልፍ ምዕራፍን እንደሚከፍት አስታውቀዋል። ከንግድ ባንክ ጋር በመሆን ኢትዮጵያውያን በዓለም አቀፍ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንዲሳተፉ የሚያስችላቸው አስተማማኝ ዲጂታል የክፍያ መፍትሄ መቅረቡ የሚያኮራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በቀጣይ ማስተር ካርድ ከባንኩ ጋር ዲጂታል ቴክኖሎጂን የማሳደግ ስራ ላይ በጋራ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
የሚታይ
ጉባኤው ወጣቶች የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ አፍሪካን በመገንባት ሂደት ሚናቸውን ይበልጥ እንዲያጎለብቱ የሚያግዝ ነው -ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር)
Mar 27, 2025 10
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦የፓን አፍሪካ ወጣቶች አመራር ጉባኤ ወጣቶች የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ አፍሪካን በመገንባት ሂደት ሚናቸውን ይበልጥ እንዲወጡ እንደሚያስችል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የፓን አፍሪካ ወጣቶች አመራር ጉባኤ ከመጋቢት 25 እስከ 27/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድም ተገልጿል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ አፍሪካ ከህዝቧ አብዛኛው ወጣት መሆኑን ያነሱ ሲሆን ፥ በጠንካራ ማህበራዊ እሴቶች፣ጥበባትና በተፈጥሮ ጸጋዎች የታደለች አህጉር ናት ብለዋል። ጉባኤው “የወጣቶችን አቅም ለበለፀገች አፍሪካ” በሚል መሪ ሃሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል ብለዋል። በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው ይህ አህጉራዊ ጉባኤ ዋና አላማ ወጣቶች የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ አፍሪካን በመገንባት ሂደት ውስጥ የመሪነት ሚናቸውን እንዲያበረክቱ ለማስቻል መሆኑን ጠቁመዋል። የአፍሪካ ወጣቶች ቻርተር ላይ የተደነገጉ መብቶችና ግዴታዎችን ለማስገንዘብም ጉባኤው ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል። የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤን ለወጣቱ ለማስረጽና በአፍሪካ ህብረት መሪዎች ጉባዔ የተያዘው አህጉራዊ መሻቶችን በጋራ እውን ለማድረግ ነው ብለዋል። የወጣቶችን ዲፕሎማሲ አቅም በማሳደግ ወጣቱ ከሀገሩ አልፎ በአህጉርና በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የአፍሪካን መብትና ጥቅም ማስከበር እንዲችል ጉባዔው ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል ፡፡ መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የወጣቱን ጉዳይ የዕቅዳቸው አካል አድርገው በመስራት ረገድ ለመወያየት ምቹ አጋጣሚ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት የነጻነትና የለውጥ ምሳሌ ናት ያሉት ሚኒስትሯ፥ ለአፍሪካ አንድነትና ትስስር መጠናከር ከፍተኛ ሚና እያበረከተች ያለች ሀገር መሆኗን አንስተዋል። የፓን አፍሪካን እሳቤ በመላው አፍሪካ እንዲጎለብት የወጣቱ ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በርካታ ተግባራትን በማከናወን ውጤቶች እየተመዘገቡበት የሚገኘው የመደመር እሳቤ ለፓን አፍሪካኒዝም መጎልበት በሚኖሩ እሴቶች ላይ የፓናል ውይይት እንደሚደረግም ገልጸዋል። ከዚህ ባለፈም የኢትዮጵያ ታሪክና እሴት የሚተዋወቅበትና በመዲናዋ የተሰሩ ልማቶች የሚጎበኙበት እንዲሁም የባህል ልውውጥ የሚደረግበት ፕሮግራም እንደሚኖርም ጠቁመዋል። በመድረኩ ከ53 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ አንድ ሺህ የሚሆኑ ወጣት መሪዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች፣የተለያዩ መንግስት ስራ ኃላፊዎች፣ የወጣት አደረጃጀቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንደሚሳተፉ አንስተዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ የዕውቀት፣ የሥነ-ጥበብና የኪነ-ጥበብ ቤት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Mar 27, 2025 15
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ የዕውቀት፣ የሥነ-ጥበብና የኪነ-ጥበብ ቤት ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ። ፕሬዝዳንቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ-ጥበብ እና ያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤቶችን ጎብኝተዋል።   ጉብኝታቸውም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤቶች ለዘርፉ ዕድገት እያበረከቱት ያለውን ሚና እና የስራ እንቅስቃሴያቸው ላይ ምልከታ ማድረግን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤት በአፍሪካ ደረጃ ከሚገኙ የሥነ-ጥበብ ተቋማት አንፃር ከፍ ያለ ዕውቀት የሚንሸራሸርበት ተቋም መሆኑን እንደተመለከቱ ተናግረዋል። በትምህርት ቤቱ ለሥነ-ጥበብ ስራ እና ለመማር ማስተማር ምቹ መደላድል የሚፈጥር የከባቢ ልማት እና ዘመናዊ ተቋም እየተገነባ እንደሚገኝም አንስተዋል። ለረጅም ጊዜ ተጠብቀው የቆዩ የትምህርት ቤቱ የአዕምሮ ውጤቶች አስገራሚ ናቸው ያሉት ፕሬዝዳንት ታዬ፤ ለዚህም ለዩኒቨርሲቲው አመራር፣ መምህራንና ተማሪዎች ምስጋና አቅርበዋል። የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤትም ለኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዕድገት የራሱን ጉልህ አሻራ ያሳረፈ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሙዚቃ ስራ ያለን ዋጋ ከፍ ያለ ነው ያሉት ፕሬዝዳንት ታዬ፤ ይህም ለኪነ-ጥብብ ዕድገት አበክረው የሰሩ ኢትዮጵያውያን የልፋት ውጤት መሆኑን አስገንዝበዋል።   በኢትዮጵያ የሙዚቃታሪክ ውስጥ ከድምጻውያን ባሻገር የመሳሪያ ተጫዋችና ተወዛዋዦች ተገቢውን ክብርና ዕውቅና ማግኘት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፥ ዩኒቨርሲቲው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መርሃ ግብሮች በማቀናጀት በኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ዘርፍም ሚናውን እየተወጣ ነው ብለዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በዩኒቨርሲቲው የኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤቶች ያደረጉት ጉብኝትም ስኬቶችን ለማስቀጠልና ጉድለቶችን ለማስተካከል ስንቅ መሆኑን አስረድተዋል። የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ-ጥበብና የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤቶች ለበርካታ ዓመታት በኢትዮጵያና የዓለም የሥነ-ጥበብና የኪነ-ጥበብ ሥራዎች ላይ ተጠቃሽ የሆኑ በርካታ የጥበብ ሰዎችን እያፈሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
Mar 27, 2025 16
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ ተፈራርመዋል። ስምምነቱ ኢንቨስትመንትን ለማነቃቃት የሚያስችል የሚዲያ አጋርነት እና የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ገጽታ ለማጠናከር ያለመ እንደሆነም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፥ ኮሚሽኑ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሽግግር በመምራት ሂደት ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የሀገሪቱን የኢንቨስትመንት እድሎች ማስተዋወቅ ቀዳሚ ስራው መሆኑን ተናግረዋል።   መንግስት ለኢንቨስትመንት ምቹ ምህዳር በመፍጠር በርካታ ተግባራትን ማከናወኑንም አስረድተዋል። እንዲሁም በተለያዩ ዘርፎች ወደ ሥራ የገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን የመደገፍ እና የመከታተል ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። እነዚህን ተግባራት በአግባቡ ለማስተዋወቅ የሚዲያ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፥ ስምምነቱ እምቅ አቅሞችን ለመጠቀም የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የኢንቨስትመንት መረጃዎችን በሙያዊ እውቀትና በጥራት ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም መሆኑን አንስተው ከአገልግሎቱ ጋር በመስራታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው ስምምነቱ የኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻነት ለማስፋት እንደ ትልቅ እድል የሚወሰድ ነው ብለዋል። አገልግሎቱ የኮሚሽኑ ህልሞች እውን እንዲሆኑ በዜናና ዜና ነክ የዘገባ ስራዎች የማስተዋወቅ ሚናውን እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ለዚህም የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድሎች፣ የተፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎችን እና እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ተደራሽ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
የመተባበርና የመተጋገዝ እሴትን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት በጋራ መስራት ይገባል
Mar 27, 2025 18
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦የመተባበርና የመተጋገዝ እሴትን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት በጋራ ልንሰራ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ተናገሩ። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሞሮኮ ንጉስ መሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑላሞች ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ለአንድ ሺህ አቅመ ደካሞች ማዕድ አጋርቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፥በኢትዮጵያ የሞሮኮ አምባሳደር ኔዛ አሎዩ ምሃምዲ እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ እንዳሉት፥ የመተባበርና የመተጋገዝ እሴትን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት በጋራ መስራት ይገባል። በረመዳን ጾም ለአቅመ ደካሞች የሚደረገውን የድጋፍ ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ነው የገለጹት። የሞሮኮ ንጉስ መሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑላሞች ፋውንዴሽን ላደረገው ድጋፍ አመስግነው፥ ሁላችንም ባለን አቅም መደጋገፍ አለብን ሲሉ አሳስበዋል። ምክር ቤቱ ተቋማትን በማስተባበር በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ስደተኞችን ጨምሮ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የኢፍጣር መርሃ ግብር ሲያካሂድ መቆየቱን ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ የሞሮኮ አምባሳደር ኔዛ አሎዩ ምሃምዲ በበኩላቸው፥ ፋውንዴሽኑ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉ ለኢትዮጵያ ያለንን ቅርበትና ወዳጅነት የሚያሳይ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ፋውንዴሽኑ ከተቋቋመ አንስቶ በተለያዩ አገራት ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች እያገዘ እንደሚገኝ በመጠቆም ዛሬ የተደረገው ድጋፍ ሞሮኮ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ወዳጅነትና ትብብር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይ ሞሮኮ በማህበራዊ እና ሰብዓዊ ትብብሮች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ወዳጅነት አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል። እገዛውን ያገኙ ወገኖች ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው የረመዳን ወር ሁሉም ለሰላም የሚተጋበትና ባለው አቅም የተቸገሩትን የሚረዳበት ነው ብለዋል።
ባንኩ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ የፋይናንስ አገልግሎቶች ማቅረቡን ያጠናክራል- አቤ ሳኖ
Mar 27, 2025 38
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የባንኩ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከማስተር ካርድ ጋር በመተባበር ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ ዓለም አቀፍ የዲጂታል ክፍያዎችን ማድረስ የሚያስችሉ ፕላስቲክ እና ቨርቹዋል ቅድመ ክፍያ ማስተር ካርዶችን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ ባንኩ የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት በዲጂታል ፋይናንስ ላይ ትኩረት ያደረጉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከዚህም መካከል አዳዲስ አስተማማኝ የፋይናንስ ዲጂታል ቅድመ ክፍያ አገልግሎቶችን ለደንበኞቹ ለማቅረብ እያከናወነ የሚገኘውን ተግባራትን አንስተዋል፡፡ ባንኩ ዛሬ ይፋ ያደረገው ዓለም አቀፍ ፕላስቲክ እና ቨርቹዋል ቅድመ ክፍያ ካርዶች አዳዲስ እና አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለደንበኞች ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል፡፡ ዲጂታል የቅድመ ክፍያ ካርዶች በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ነጋዴዎች ተቀባይነት ያላቸው መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፥ ክፍያ ካርዶች የባንኩን የላቀ የደህንነት እርምጃዎች የሚያሳዩ መሆኑንም ተናግረዋል። በቀጣይ ባንኩ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት ለመመለስ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ የዓለም አቀፍ ዲጂታል ክፍያዎችን ተደራሽ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የማስተር አፍሪካ ፕሬዝዳንት ማርክ ኤሊዮት በበኩላቸው፤ በንግድ ባንክ ይፋ የተደረገውን የቅድመ ክፍያ ዲጂታል ማስተር ካርድ በታዳጊ የአፍሪካ ገበያዎች ለማሳደግ ለያዘው ስትራቴጂ ቁልፍ ምዕራፍን እንደሚከፍት አስታውቀዋል። ከንግድ ባንክ ጋር በመሆን ኢትዮጵያውያን በዓለም አቀፍ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንዲሳተፉ የሚያስችላቸው አስተማማኝ ዲጂታል የክፍያ መፍትሄ መቅረቡ የሚያኮራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በቀጣይ ማስተር ካርድ ከባንኩ ጋር ዲጂታል ቴክኖሎጂን የማሳደግ ስራ ላይ በጋራ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሳታፊና ጤናማ ፉክክር የሚታይበት የፖለቲካ አውድ እየተፈጠረ ነው
Mar 27, 2025 42
አሶሳ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በመፈጠሩ አሳታፊና ጤናማ ፉክክር የሚታይበት የፖለቲካ አውድ እየተፈጠረ መሆኑን የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። የምክርቤቱ ሰብሳቢና የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ቤህነን) ፓርቲ ሊቀመንበር አብዱሰላም ሸንገል፤ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተለይም በክልሉ ያለውን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በክልሉ 10 የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የጠቀሱት አብዱሰላም፤ የዚህ ተሳትፎ መሰረቱ የፖለቲካ ምህዳሩ እየሰፋና በሃሳብ የበላይነት በክርክር የሚያምን ትውልድ እየተፈጠረ በመምጣቱ መሆኑን ተናግረዋል። ከለውጡ በፊት የተፎካካሪ ፓርቲ አደረጃጀቱን ለማስፋት ከባድ ፈተና እንደነበር አስታውሰው አሁን ግን የፖለቲካ ምህዳሩ እየሰፋ የፖለቲካ ፓርቲ የመደራጀትና አባላትን ማፍራት የሚችልበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። በክልሉ ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በመፈጠሩ አሳታፊና ፉክክር የሚታይበት የፖለቲካ አውድ እየተፈጠረ ይገኛልም ነው ያሉት። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከገዢው ፓርቲ ጋር በክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ በሀሳብ እየተከራከሩ አብሮ የመስራት ልምድ እየዳበረ ስለመሆኑም አንስተዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ዋነኛ ዓላማ የህዝብን አንድነት ማጠናከር፣ የሀገሪቱን ሰላምና ልማትን ማስቀጠል መሆኑን ጠቅሰው በሀገር ብሄራዊ ጥቅምና ሉአላዊነት ላይ ልዩነት ሊኖር አይገባም ብለዋል። በክልሉ የመንግስት ኃላፊነት ላይ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ስልጣን ይዘው እየሰሩ መሆኑንና ለአብነትም እሳቸው የካቢኔ አባል እንደሆኑ ገልጸዋል። የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት ከክልሉ መንግስት ጋር ውይይት ለማድረግ በሚፈልግበት ጊዜ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን እና የሚያጋጥሙ ችግሮችን በንግግር እየፈቱ መሆኑንም ተናግረዋል። የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሃሳብ እና ሰላማዊ መንገድን ተጠቅመው ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት እያደረጉት ያለውን ተሳትፎ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
ኢትዮጵያ ህገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመቆጣጠር በቁርጠኝነት እየሰራች ነው-አምባሳደር ባጫ ደበሌ
Mar 27, 2025 34
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በቀጣናው እና በአፍሪካ ህገወጥ የቀላል መሳሪያ ዝውውር ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በቁርጠኝነት እየሰራች እንደምትገኝ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ገለጹ። አምባሳደር ባጫ ደበሌ ከቀጣናዊ የቀላል የጦር መሳሪያ ቁጥጥር ማዕከል ዋና ፀሐፊ ጂን ፒዬር ቤቲንዲጅ ጋር ዛሬ በናይሮቢ ተወያይተዋል። ውይይቱ ማዕከሉ በቀጣናው ህገ ወጥ የቀላል የጦር መሳሪያዎች እና አነስተኛ ትጥቆች ዝውውር የመቆጣጠር አቅሙን ማሳደግ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። አምባሳደር ባጫ ኢትዮጵያ በቀጣናው ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ቁርጠኝነት እንዳላት ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ህገወጥ የአነስተኛ ጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመቆጣጠር እየተደረገ ባለው ጥረት ያላትን ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል አመልክተዋል። የቀጣናዊ የቀላል የጦር መሳሪያ ቁጥጥር ማዕከል (RECSA) ዋና ፀሐፊ ጂን ፒዬር ቤቲንዲጅ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ለማሳደግ ያላትን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው እና አፍሪካ ህገ ወጥ የቀላል የጦር መሳሪያዎች ዝውውር በመቆጣጠር ጥረቶች ውስጥ ቁልፍ አጋር መሆኗን በናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያ የህገወጥ መሳሪያ ዝውውር ቁጥጥር ማድረግ ለደህንነት እና ዘላቂ ልማት መረጋጋጥ ከፍተኛ ሚና እንዳለው በጽኑ እንደምታምንም ተገልጿል።
በክልሉ ለሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት በተሰሩ ስራዎች አንጻራዊ ሰላም ማስፈን ተችሏል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
Mar 27, 2025 70
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፦ በክልሉ ለሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት በተሰሩ ስራዎች አንጻራዊ ሰላም ማስፈን ተችሏል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች ጋር በሰላምና ፀጥታ ዙሪያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ያደረጉት ምክክር ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ ማጠቃለያ እንደገለፁት፤ ኢ-ተገማች በሆነው የአለም ሁኔታ ክልላዊ፤ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታን ፈጥኖ በመረዳት ሁሌም ቀድሞ ለመገኘት ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል። የክልሉ መንግስት ለሰላምና ፀጥታው ዘርፍ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት ባከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ስራዎች በክልሉ አንጻራዊ ሰላም ማስፈን መቻሉን ጠቅሰው፤ ይህም ክልሉ ከልማት ስራዎች ባሻገር ትልልቅ ሀገራዊ ኩነቶችን በስኬት ማስተናገድ ማስቻሉን ገልጸዋል፡፡ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በክልሉ በሰላም በኩል የተመዘገበው ስኬት የኢንቨስትመንት ፍሰትና የቱሪዝም ዘርፍን በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት ለፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ለዘላቂ ልማት ምቹ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም በክልሉ በሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ለተመዘገበው አመርቂ ውጤት ህብረተሰቡ እና የፀጥታ ሀይሉ ሊመሰገኑ ይገባል ማለታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል። ሰላም በጊዜና በቦታ ሳይገደብ ሁሌም የሁሉም ነገር ቀዳሚ ተግባር መሆኑን ጠቁመው፤ የፖሊስ መኮንኖች ነፃና ገለልተኛ ሆነው፤ ሞያዊ ስነምግባሩን በተግባር በመላበስና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት ህብረተሰቡን በቅንነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት፡፡ በቀጣይም ጊዜያዊና ወቅታዊ ፈተናዎችን በብቃት መሻገር የሚችል የፖሊስ ሰራዊት እና ጠንካራ ተቋም ለመገንባት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ተናግረዋል። ከነባራዊ ሁኔታዎች አኳያ ዕቅዶችን መከለስ፤ በጠንካራ ተቋማዊ አሰራር መምራትና መፈፀም፤ ሞያዊ ስነምግባርን ጠብቆ ለሕግና ለሕገመንግስታዊ ስርዓቱ ታማኝ በመሆንና ከህብረተሰቡ ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ በመስራት የተጀመሩ የሰላም ግንባታ ተግባራትን ከግብ ማድረስ ይገባል ነው ያሉት። የሽግግር ፍትህ ስራዎች ትግበራን መከታተልና የጠንካራ ተቋም ግንባታ ስራዎችን በማጠናከር የዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል። የዲጂታል ዘመኑን በዋጀ አግባብ የሰላምና ፀጥታውን ዘርፍ የመረጃ ስርዓት ማዘመንና በነባራዊ ሁኔታዎች ግምገማና ሳይንሳዊ የመረጃ ትንተናን መሠረት ባደረገ መልኩ ህግ የማስከበር ዝግጁነትን ማሳደግ ይገባል ብለዋል። የሚዲያ አውታሮችን በህዝቦች መካከል ጥርጣሬን፤ ጥላቻንና ግጭትን ለመቀስቀስ በመጠቀም የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ በሚሰሩ አካላት ላይ ህጋዊ አስተማሪ ዕርምጃዎችን በመውሰድ የህግ የበላይነትን በሁሉም መስክ በሙላት ለማረጋገጥ መስራት ይገባል ነው ያሉት። ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ገቢ ፍታሃዊ ግብር በመሰብሰብ የልማት ስራዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን መስራት የሁሉም የጋራ ኃላፊነት በመሆኑ ገቢ አሰባሰብ ስራዎችን በማገዝ ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑንም ገልጸዋል። ሀገር በቀል የሰላም ግንባታ ተቋማትንና ህዝባዊ አቅሞችን በአግባቡ በመጠቀም በቀጣይም የክልሉን ሰላም ለማፅናት መስራት እንደሚገባም አክለዋል። በአጠቃላይ የፖሊስ ሀይሉ ከተሰጠው በላይ በመስራትና ከሚጠበቀው በላይ ፈፅሞ በመገኘት በታሪክ ተወዳሽ ለመሆን ሀላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንደሚገባ አቅጣጫዎች ማስቀመጣቸውም ተገልጿል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደርን ተቀብለው አነጋገሩ
Mar 26, 2025 84
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፡- የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሤን(ዶ/ር) በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። ውይይታቸው የኢትዮጵያን እና የእስራኤልን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል።   በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሤ(ዶ/ር) ከፕሬዝዳንት ታዬ ጋር የነበራቸውን ውይይት በተመለከተ ለኢዜአ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በውይይታችን የኢትዮጵያ እና እስራኤል ግንኙነት ልዩ፣ ጥልቅ እና ታሪካዊ መሆኑን አንስተናል ብለዋል። ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በደን ልማት፣ በቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ በሞደርናይዜሽን እና በጤና ዘርፎች በትብብር እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም እስራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዘርፈ ብዙ የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የባንግላዲሽ አምባሳደር አሰናበቱ
Mar 26, 2025 68
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፡- የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የባንግላዲሽ አምባሳደር ሲክደር ቦዲሩዝማንን አሰናበቱ። አምባሳደር ሲክደር ቦዲሩዝማን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ እጅግ ደስተኛ እንደነበሩ አንስተዋል። ኢትዮጵያ ታሪካዊና ቀደምት ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ በቆይታቸው ኢትዮጵያውያን እንግዳ ተቀባይ መሆናቸውንና ሀገሪቱም ለኑሮ ተስማሚና ምቹ መሆኗን ተመልክቻለሁ ብለዋል።   ኢትዮጵያ የአፍሪካ ማዕከል ነች ያሉት አምባሳደሩ፤ የአፍሪካ ህብረት መስራች መሆኗን ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለቤት መሆኗና የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷ የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል። በመሆኑም ባንግላዲሽ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ አቋም እንዳላትም አረጋግጠዋል። በቆይታቸውም የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ግንኙነት የሚያጠናክሩ ተግባራት ማከናወናቸውን ገልጸዋል። ለአብነትም በኢኮኖሚና በህዝብ ለህዝብ ትስስርና መሰል ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ነው ያሉት። በቀጣይም የባንግላዲሽና የኢትዮጵያ ግንኙነት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
በለውጡ በተወሰዱ እርምጃዎች በሠላም ግንባታ ዘርፍ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸው ተገለጸ
Mar 26, 2025 74
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በለውጡ በተወሰዱ እርምጃዎች አማካኝነት በሠላም ግንባታ ዘርፍ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ በወቅታዊ ሁኔታ በሰጡት መግለጫ በክልሉ የታየው አዎንታዊ ሠላም ሀገር በቀል እሳቤዎችን መሰረት ያደረገ የግጭት አፈታት ስልት የመጠቀማችን ውጤት ነው ብለዋል። ባለፉት ጊዜያት በኢትዮጵያ የተሳሳቱ ትርክቶችን በማረም ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በሚያጎለብት መልኩ ዘላቂና አዎንታዊ ሠላም እንዲገነባ ብዙ ስራ መሰራቱን አንስተዋል ። ክልላችንም በአዲስ መልክ ከተዋቀረ ጊዜ ጀምሮ በሠላምና ፀጥታ ዘርፍ በርካታ ስራዎችን ሰርተናል ብለዋል አቶ አንድነት አሸናፊ። ክልሉ ሲመሠረት በአብዛኛዎቹ አካባቢዎች የሰላም ሁኔታ አስቸጋሪ እንደነበረና በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ደግሞ ችግሩ ከፍ ያለ እንደነበረም ጠቅሰዋል። ባለፉት ሶስት ዓመት ተኩል የሠላምና ፀጥታ ስራ በመከናወኑ ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን አስረድተዋል። በክልሉ በምዕራብ ኦሞ፣ የሸካና የቤንች ሸኮ ዞኖች የተፈጠረውን ግጭትን፣ ሞትና መፈናቀልን ለማስቆም በዋናነት ትኩረት ተደርጎ የተሰራበት መሆኑንና የተስተጓጎሉ የህዝብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተግባራትና የመንግሥት የስራ እንቅስቃሴዎች ዳግም ወደ ስራ እንዲገቡ የማድረግ ስራ በሰፊው መሠራቱን ጠቁመዋል፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ህዝቡ በሠላም ወጥቶ በሠላም የሚገባበት ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ግጭቶችን ሙሉ በሙሉ ማስቆም ተችሏል ያሉት ኃላፊው በህዝቦች ዘንድ የነበረው ትስስር፣ አንድነት እና ወንድማማችነት እንዲጎለብት መሰራቱን ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም የህዝቡ ማህበራዊ እሴቶች ሀገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ሚና በእጅጉ ከፍተኛ ስለመሆኑ መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል። በክልሉ ይቅርታ ማድረጊያ መንገዶችን በመለየትና ጫካ የገቡ አካላት ትጥቆቻቸውን በመፍታት በሠላማዊ መንገድ እጅ እንዲሰጡ በማድረግ፤ በባህላዊ መንገድ ይቅርታ ተደርጎላቸው የተለያዩ ስልጠናዎችን ወስደው ሰላማዊ ህይወት እንዲጀምሩ መደረጉን ገልጸዋል። አሁን ባለንበት ሁኔታ የህዝቦች የወንድማማችነት እና የእህታማማችነት እሳቤ ጎልብቶ በሁሉም አካባቢ ሠላም እንዲረጋገጥ ተደርጓል ብለዋል፡፡
ፖለቲካ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሳታፊና ጤናማ ፉክክር የሚታይበት የፖለቲካ አውድ እየተፈጠረ ነው
Mar 27, 2025 42
አሶሳ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በመፈጠሩ አሳታፊና ጤናማ ፉክክር የሚታይበት የፖለቲካ አውድ እየተፈጠረ መሆኑን የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። የምክርቤቱ ሰብሳቢና የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ቤህነን) ፓርቲ ሊቀመንበር አብዱሰላም ሸንገል፤ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተለይም በክልሉ ያለውን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በክልሉ 10 የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የጠቀሱት አብዱሰላም፤ የዚህ ተሳትፎ መሰረቱ የፖለቲካ ምህዳሩ እየሰፋና በሃሳብ የበላይነት በክርክር የሚያምን ትውልድ እየተፈጠረ በመምጣቱ መሆኑን ተናግረዋል። ከለውጡ በፊት የተፎካካሪ ፓርቲ አደረጃጀቱን ለማስፋት ከባድ ፈተና እንደነበር አስታውሰው አሁን ግን የፖለቲካ ምህዳሩ እየሰፋ የፖለቲካ ፓርቲ የመደራጀትና አባላትን ማፍራት የሚችልበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። በክልሉ ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በመፈጠሩ አሳታፊና ፉክክር የሚታይበት የፖለቲካ አውድ እየተፈጠረ ይገኛልም ነው ያሉት። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከገዢው ፓርቲ ጋር በክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ በሀሳብ እየተከራከሩ አብሮ የመስራት ልምድ እየዳበረ ስለመሆኑም አንስተዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ዋነኛ ዓላማ የህዝብን አንድነት ማጠናከር፣ የሀገሪቱን ሰላምና ልማትን ማስቀጠል መሆኑን ጠቅሰው በሀገር ብሄራዊ ጥቅምና ሉአላዊነት ላይ ልዩነት ሊኖር አይገባም ብለዋል። በክልሉ የመንግስት ኃላፊነት ላይ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ስልጣን ይዘው እየሰሩ መሆኑንና ለአብነትም እሳቸው የካቢኔ አባል እንደሆኑ ገልጸዋል። የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት ከክልሉ መንግስት ጋር ውይይት ለማድረግ በሚፈልግበት ጊዜ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን እና የሚያጋጥሙ ችግሮችን በንግግር እየፈቱ መሆኑንም ተናግረዋል። የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሃሳብ እና ሰላማዊ መንገድን ተጠቅመው ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት እያደረጉት ያለውን ተሳትፎ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
ኢትዮጵያ ህገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመቆጣጠር በቁርጠኝነት እየሰራች ነው-አምባሳደር ባጫ ደበሌ
Mar 27, 2025 34
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በቀጣናው እና በአፍሪካ ህገወጥ የቀላል መሳሪያ ዝውውር ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በቁርጠኝነት እየሰራች እንደምትገኝ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ገለጹ። አምባሳደር ባጫ ደበሌ ከቀጣናዊ የቀላል የጦር መሳሪያ ቁጥጥር ማዕከል ዋና ፀሐፊ ጂን ፒዬር ቤቲንዲጅ ጋር ዛሬ በናይሮቢ ተወያይተዋል። ውይይቱ ማዕከሉ በቀጣናው ህገ ወጥ የቀላል የጦር መሳሪያዎች እና አነስተኛ ትጥቆች ዝውውር የመቆጣጠር አቅሙን ማሳደግ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። አምባሳደር ባጫ ኢትዮጵያ በቀጣናው ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ቁርጠኝነት እንዳላት ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ህገወጥ የአነስተኛ ጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመቆጣጠር እየተደረገ ባለው ጥረት ያላትን ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል አመልክተዋል። የቀጣናዊ የቀላል የጦር መሳሪያ ቁጥጥር ማዕከል (RECSA) ዋና ፀሐፊ ጂን ፒዬር ቤቲንዲጅ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ለማሳደግ ያላትን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው እና አፍሪካ ህገ ወጥ የቀላል የጦር መሳሪያዎች ዝውውር በመቆጣጠር ጥረቶች ውስጥ ቁልፍ አጋር መሆኗን በናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያ የህገወጥ መሳሪያ ዝውውር ቁጥጥር ማድረግ ለደህንነት እና ዘላቂ ልማት መረጋጋጥ ከፍተኛ ሚና እንዳለው በጽኑ እንደምታምንም ተገልጿል።
በክልሉ ለሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት በተሰሩ ስራዎች አንጻራዊ ሰላም ማስፈን ተችሏል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
Mar 27, 2025 70
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፦ በክልሉ ለሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት በተሰሩ ስራዎች አንጻራዊ ሰላም ማስፈን ተችሏል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች ጋር በሰላምና ፀጥታ ዙሪያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ያደረጉት ምክክር ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ ማጠቃለያ እንደገለፁት፤ ኢ-ተገማች በሆነው የአለም ሁኔታ ክልላዊ፤ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታን ፈጥኖ በመረዳት ሁሌም ቀድሞ ለመገኘት ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል። የክልሉ መንግስት ለሰላምና ፀጥታው ዘርፍ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት ባከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ስራዎች በክልሉ አንጻራዊ ሰላም ማስፈን መቻሉን ጠቅሰው፤ ይህም ክልሉ ከልማት ስራዎች ባሻገር ትልልቅ ሀገራዊ ኩነቶችን በስኬት ማስተናገድ ማስቻሉን ገልጸዋል፡፡ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በክልሉ በሰላም በኩል የተመዘገበው ስኬት የኢንቨስትመንት ፍሰትና የቱሪዝም ዘርፍን በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት ለፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ለዘላቂ ልማት ምቹ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም በክልሉ በሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ለተመዘገበው አመርቂ ውጤት ህብረተሰቡ እና የፀጥታ ሀይሉ ሊመሰገኑ ይገባል ማለታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል። ሰላም በጊዜና በቦታ ሳይገደብ ሁሌም የሁሉም ነገር ቀዳሚ ተግባር መሆኑን ጠቁመው፤ የፖሊስ መኮንኖች ነፃና ገለልተኛ ሆነው፤ ሞያዊ ስነምግባሩን በተግባር በመላበስና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት ህብረተሰቡን በቅንነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት፡፡ በቀጣይም ጊዜያዊና ወቅታዊ ፈተናዎችን በብቃት መሻገር የሚችል የፖሊስ ሰራዊት እና ጠንካራ ተቋም ለመገንባት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ተናግረዋል። ከነባራዊ ሁኔታዎች አኳያ ዕቅዶችን መከለስ፤ በጠንካራ ተቋማዊ አሰራር መምራትና መፈፀም፤ ሞያዊ ስነምግባርን ጠብቆ ለሕግና ለሕገመንግስታዊ ስርዓቱ ታማኝ በመሆንና ከህብረተሰቡ ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ በመስራት የተጀመሩ የሰላም ግንባታ ተግባራትን ከግብ ማድረስ ይገባል ነው ያሉት። የሽግግር ፍትህ ስራዎች ትግበራን መከታተልና የጠንካራ ተቋም ግንባታ ስራዎችን በማጠናከር የዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል። የዲጂታል ዘመኑን በዋጀ አግባብ የሰላምና ፀጥታውን ዘርፍ የመረጃ ስርዓት ማዘመንና በነባራዊ ሁኔታዎች ግምገማና ሳይንሳዊ የመረጃ ትንተናን መሠረት ባደረገ መልኩ ህግ የማስከበር ዝግጁነትን ማሳደግ ይገባል ብለዋል። የሚዲያ አውታሮችን በህዝቦች መካከል ጥርጣሬን፤ ጥላቻንና ግጭትን ለመቀስቀስ በመጠቀም የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ በሚሰሩ አካላት ላይ ህጋዊ አስተማሪ ዕርምጃዎችን በመውሰድ የህግ የበላይነትን በሁሉም መስክ በሙላት ለማረጋገጥ መስራት ይገባል ነው ያሉት። ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ገቢ ፍታሃዊ ግብር በመሰብሰብ የልማት ስራዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን መስራት የሁሉም የጋራ ኃላፊነት በመሆኑ ገቢ አሰባሰብ ስራዎችን በማገዝ ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑንም ገልጸዋል። ሀገር በቀል የሰላም ግንባታ ተቋማትንና ህዝባዊ አቅሞችን በአግባቡ በመጠቀም በቀጣይም የክልሉን ሰላም ለማፅናት መስራት እንደሚገባም አክለዋል። በአጠቃላይ የፖሊስ ሀይሉ ከተሰጠው በላይ በመስራትና ከሚጠበቀው በላይ ፈፅሞ በመገኘት በታሪክ ተወዳሽ ለመሆን ሀላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንደሚገባ አቅጣጫዎች ማስቀመጣቸውም ተገልጿል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደርን ተቀብለው አነጋገሩ
Mar 26, 2025 84
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፡- የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሤን(ዶ/ር) በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። ውይይታቸው የኢትዮጵያን እና የእስራኤልን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል።   በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሤ(ዶ/ር) ከፕሬዝዳንት ታዬ ጋር የነበራቸውን ውይይት በተመለከተ ለኢዜአ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በውይይታችን የኢትዮጵያ እና እስራኤል ግንኙነት ልዩ፣ ጥልቅ እና ታሪካዊ መሆኑን አንስተናል ብለዋል። ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በደን ልማት፣ በቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ በሞደርናይዜሽን እና በጤና ዘርፎች በትብብር እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም እስራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዘርፈ ብዙ የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የባንግላዲሽ አምባሳደር አሰናበቱ
Mar 26, 2025 68
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፡- የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የባንግላዲሽ አምባሳደር ሲክደር ቦዲሩዝማንን አሰናበቱ። አምባሳደር ሲክደር ቦዲሩዝማን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ እጅግ ደስተኛ እንደነበሩ አንስተዋል። ኢትዮጵያ ታሪካዊና ቀደምት ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ በቆይታቸው ኢትዮጵያውያን እንግዳ ተቀባይ መሆናቸውንና ሀገሪቱም ለኑሮ ተስማሚና ምቹ መሆኗን ተመልክቻለሁ ብለዋል።   ኢትዮጵያ የአፍሪካ ማዕከል ነች ያሉት አምባሳደሩ፤ የአፍሪካ ህብረት መስራች መሆኗን ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለቤት መሆኗና የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷ የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል። በመሆኑም ባንግላዲሽ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ አቋም እንዳላትም አረጋግጠዋል። በቆይታቸውም የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ግንኙነት የሚያጠናክሩ ተግባራት ማከናወናቸውን ገልጸዋል። ለአብነትም በኢኮኖሚና በህዝብ ለህዝብ ትስስርና መሰል ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ነው ያሉት። በቀጣይም የባንግላዲሽና የኢትዮጵያ ግንኙነት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
በለውጡ በተወሰዱ እርምጃዎች በሠላም ግንባታ ዘርፍ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸው ተገለጸ
Mar 26, 2025 74
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በለውጡ በተወሰዱ እርምጃዎች አማካኝነት በሠላም ግንባታ ዘርፍ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ በወቅታዊ ሁኔታ በሰጡት መግለጫ በክልሉ የታየው አዎንታዊ ሠላም ሀገር በቀል እሳቤዎችን መሰረት ያደረገ የግጭት አፈታት ስልት የመጠቀማችን ውጤት ነው ብለዋል። ባለፉት ጊዜያት በኢትዮጵያ የተሳሳቱ ትርክቶችን በማረም ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በሚያጎለብት መልኩ ዘላቂና አዎንታዊ ሠላም እንዲገነባ ብዙ ስራ መሰራቱን አንስተዋል ። ክልላችንም በአዲስ መልክ ከተዋቀረ ጊዜ ጀምሮ በሠላምና ፀጥታ ዘርፍ በርካታ ስራዎችን ሰርተናል ብለዋል አቶ አንድነት አሸናፊ። ክልሉ ሲመሠረት በአብዛኛዎቹ አካባቢዎች የሰላም ሁኔታ አስቸጋሪ እንደነበረና በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ደግሞ ችግሩ ከፍ ያለ እንደነበረም ጠቅሰዋል። ባለፉት ሶስት ዓመት ተኩል የሠላምና ፀጥታ ስራ በመከናወኑ ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን አስረድተዋል። በክልሉ በምዕራብ ኦሞ፣ የሸካና የቤንች ሸኮ ዞኖች የተፈጠረውን ግጭትን፣ ሞትና መፈናቀልን ለማስቆም በዋናነት ትኩረት ተደርጎ የተሰራበት መሆኑንና የተስተጓጎሉ የህዝብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተግባራትና የመንግሥት የስራ እንቅስቃሴዎች ዳግም ወደ ስራ እንዲገቡ የማድረግ ስራ በሰፊው መሠራቱን ጠቁመዋል፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ህዝቡ በሠላም ወጥቶ በሠላም የሚገባበት ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ግጭቶችን ሙሉ በሙሉ ማስቆም ተችሏል ያሉት ኃላፊው በህዝቦች ዘንድ የነበረው ትስስር፣ አንድነት እና ወንድማማችነት እንዲጎለብት መሰራቱን ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም የህዝቡ ማህበራዊ እሴቶች ሀገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ሚና በእጅጉ ከፍተኛ ስለመሆኑ መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል። በክልሉ ይቅርታ ማድረጊያ መንገዶችን በመለየትና ጫካ የገቡ አካላት ትጥቆቻቸውን በመፍታት በሠላማዊ መንገድ እጅ እንዲሰጡ በማድረግ፤ በባህላዊ መንገድ ይቅርታ ተደርጎላቸው የተለያዩ ስልጠናዎችን ወስደው ሰላማዊ ህይወት እንዲጀምሩ መደረጉን ገልጸዋል። አሁን ባለንበት ሁኔታ የህዝቦች የወንድማማችነት እና የእህታማማችነት እሳቤ ጎልብቶ በሁሉም አካባቢ ሠላም እንዲረጋገጥ ተደርጓል ብለዋል፡፡
ማህበራዊ
ጉባኤው ወጣቶች የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ አፍሪካን በመገንባት ሂደት ሚናቸውን ይበልጥ እንዲያጎለብቱ የሚያግዝ ነው -ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር)
Mar 27, 2025 10
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦የፓን አፍሪካ ወጣቶች አመራር ጉባኤ ወጣቶች የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ አፍሪካን በመገንባት ሂደት ሚናቸውን ይበልጥ እንዲወጡ እንደሚያስችል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የፓን አፍሪካ ወጣቶች አመራር ጉባኤ ከመጋቢት 25 እስከ 27/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድም ተገልጿል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ አፍሪካ ከህዝቧ አብዛኛው ወጣት መሆኑን ያነሱ ሲሆን ፥ በጠንካራ ማህበራዊ እሴቶች፣ጥበባትና በተፈጥሮ ጸጋዎች የታደለች አህጉር ናት ብለዋል። ጉባኤው “የወጣቶችን አቅም ለበለፀገች አፍሪካ” በሚል መሪ ሃሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል ብለዋል። በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው ይህ አህጉራዊ ጉባኤ ዋና አላማ ወጣቶች የበለጸገችና ሰላሟ የተረጋገጠ አፍሪካን በመገንባት ሂደት ውስጥ የመሪነት ሚናቸውን እንዲያበረክቱ ለማስቻል መሆኑን ጠቁመዋል። የአፍሪካ ወጣቶች ቻርተር ላይ የተደነገጉ መብቶችና ግዴታዎችን ለማስገንዘብም ጉባኤው ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል። የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤን ለወጣቱ ለማስረጽና በአፍሪካ ህብረት መሪዎች ጉባዔ የተያዘው አህጉራዊ መሻቶችን በጋራ እውን ለማድረግ ነው ብለዋል። የወጣቶችን ዲፕሎማሲ አቅም በማሳደግ ወጣቱ ከሀገሩ አልፎ በአህጉርና በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የአፍሪካን መብትና ጥቅም ማስከበር እንዲችል ጉባዔው ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል ፡፡ መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የወጣቱን ጉዳይ የዕቅዳቸው አካል አድርገው በመስራት ረገድ ለመወያየት ምቹ አጋጣሚ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት የነጻነትና የለውጥ ምሳሌ ናት ያሉት ሚኒስትሯ፥ ለአፍሪካ አንድነትና ትስስር መጠናከር ከፍተኛ ሚና እያበረከተች ያለች ሀገር መሆኗን አንስተዋል። የፓን አፍሪካን እሳቤ በመላው አፍሪካ እንዲጎለብት የወጣቱ ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በርካታ ተግባራትን በማከናወን ውጤቶች እየተመዘገቡበት የሚገኘው የመደመር እሳቤ ለፓን አፍሪካኒዝም መጎልበት በሚኖሩ እሴቶች ላይ የፓናል ውይይት እንደሚደረግም ገልጸዋል። ከዚህ ባለፈም የኢትዮጵያ ታሪክና እሴት የሚተዋወቅበትና በመዲናዋ የተሰሩ ልማቶች የሚጎበኙበት እንዲሁም የባህል ልውውጥ የሚደረግበት ፕሮግራም እንደሚኖርም ጠቁመዋል። በመድረኩ ከ53 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ አንድ ሺህ የሚሆኑ ወጣት መሪዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች፣የተለያዩ መንግስት ስራ ኃላፊዎች፣ የወጣት አደረጃጀቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንደሚሳተፉ አንስተዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ የዕውቀት፣ የሥነ-ጥበብና የኪነ-ጥበብ ቤት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Mar 27, 2025 15
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ የዕውቀት፣ የሥነ-ጥበብና የኪነ-ጥበብ ቤት ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ። ፕሬዝዳንቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ-ጥበብ እና ያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤቶችን ጎብኝተዋል።   ጉብኝታቸውም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤቶች ለዘርፉ ዕድገት እያበረከቱት ያለውን ሚና እና የስራ እንቅስቃሴያቸው ላይ ምልከታ ማድረግን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤት በአፍሪካ ደረጃ ከሚገኙ የሥነ-ጥበብ ተቋማት አንፃር ከፍ ያለ ዕውቀት የሚንሸራሸርበት ተቋም መሆኑን እንደተመለከቱ ተናግረዋል። በትምህርት ቤቱ ለሥነ-ጥበብ ስራ እና ለመማር ማስተማር ምቹ መደላድል የሚፈጥር የከባቢ ልማት እና ዘመናዊ ተቋም እየተገነባ እንደሚገኝም አንስተዋል። ለረጅም ጊዜ ተጠብቀው የቆዩ የትምህርት ቤቱ የአዕምሮ ውጤቶች አስገራሚ ናቸው ያሉት ፕሬዝዳንት ታዬ፤ ለዚህም ለዩኒቨርሲቲው አመራር፣ መምህራንና ተማሪዎች ምስጋና አቅርበዋል። የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤትም ለኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዕድገት የራሱን ጉልህ አሻራ ያሳረፈ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሙዚቃ ስራ ያለን ዋጋ ከፍ ያለ ነው ያሉት ፕሬዝዳንት ታዬ፤ ይህም ለኪነ-ጥብብ ዕድገት አበክረው የሰሩ ኢትዮጵያውያን የልፋት ውጤት መሆኑን አስገንዝበዋል።   በኢትዮጵያ የሙዚቃታሪክ ውስጥ ከድምጻውያን ባሻገር የመሳሪያ ተጫዋችና ተወዛዋዦች ተገቢውን ክብርና ዕውቅና ማግኘት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፥ ዩኒቨርሲቲው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መርሃ ግብሮች በማቀናጀት በኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ዘርፍም ሚናውን እየተወጣ ነው ብለዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በዩኒቨርሲቲው የኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤቶች ያደረጉት ጉብኝትም ስኬቶችን ለማስቀጠልና ጉድለቶችን ለማስተካከል ስንቅ መሆኑን አስረድተዋል። የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ-ጥበብና የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤቶች ለበርካታ ዓመታት በኢትዮጵያና የዓለም የሥነ-ጥበብና የኪነ-ጥበብ ሥራዎች ላይ ተጠቃሽ የሆኑ በርካታ የጥበብ ሰዎችን እያፈሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የመተባበርና የመተጋገዝ እሴትን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት በጋራ መስራት ይገባል
Mar 27, 2025 18
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦የመተባበርና የመተጋገዝ እሴትን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት በጋራ ልንሰራ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ተናገሩ። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሞሮኮ ንጉስ መሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑላሞች ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ለአንድ ሺህ አቅመ ደካሞች ማዕድ አጋርቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፥በኢትዮጵያ የሞሮኮ አምባሳደር ኔዛ አሎዩ ምሃምዲ እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ እንዳሉት፥ የመተባበርና የመተጋገዝ እሴትን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት በጋራ መስራት ይገባል። በረመዳን ጾም ለአቅመ ደካሞች የሚደረገውን የድጋፍ ሥራ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ነው የገለጹት። የሞሮኮ ንጉስ መሀመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑላሞች ፋውንዴሽን ላደረገው ድጋፍ አመስግነው፥ ሁላችንም ባለን አቅም መደጋገፍ አለብን ሲሉ አሳስበዋል። ምክር ቤቱ ተቋማትን በማስተባበር በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ስደተኞችን ጨምሮ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የኢፍጣር መርሃ ግብር ሲያካሂድ መቆየቱን ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ የሞሮኮ አምባሳደር ኔዛ አሎዩ ምሃምዲ በበኩላቸው፥ ፋውንዴሽኑ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉ ለኢትዮጵያ ያለንን ቅርበትና ወዳጅነት የሚያሳይ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ፋውንዴሽኑ ከተቋቋመ አንስቶ በተለያዩ አገራት ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች እያገዘ እንደሚገኝ በመጠቆም ዛሬ የተደረገው ድጋፍ ሞሮኮ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ወዳጅነትና ትብብር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይ ሞሮኮ በማህበራዊ እና ሰብዓዊ ትብብሮች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ወዳጅነት አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል። እገዛውን ያገኙ ወገኖች ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው የረመዳን ወር ሁሉም ለሰላም የሚተጋበትና ባለው አቅም የተቸገሩትን የሚረዳበት ነው ብለዋል።
የፊቼ ጫምባላላ በዓል በሰላም እንዲከበር ከጸጥታ ሀይሉ ጋር በቅንጅት እየሰራን ነው-የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች
Mar 27, 2025 29
ሀዋሳ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ) :- የሲዳማ የዘመን መለወጫ ፊቼ ጫምባላላ በዓል በሰላም እንዲከበር ከጸጥታ ሀይሉ ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የፊቼ ጫምባላላ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁንም የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት ፊቼ ጫምባላላ የሰላም፣የአብሮነት፣የመረዳዳትና የፍቅር እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር እየሰሩና በዓሉን ለመታደም የሚመጡ እንግዶችን በመቀበል ላይ ናቸው። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል የባህል አዳራሽ ክፍለ ከተማ ሐረር ቀበሌ ነዋሪ አቶ እንዳለ ተመስገን እንዳሉት፥ የፊቼ ጨምበላላ በዓልን በሰላም ለማክበር በቀበሌ ደረጃ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል። ቀደም ባሉት ቀናት ነዋሪዎቹ ከተማዋን ማጽዳታቸውንና ዛሬ ደግሞ በሲዳማ ባህል መሰረት እንግዶችን ''ዳኤ ቡሹ'' በማለት እየተቀበሉ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ሄለን ተክለሀይማኖት በበኩሏ እንግዶች የእንግድነት ስሜት ሳያድርባቸው በዓሉን አክብረው እስኪመለሱ ድረስ በመልካም ሁኔታ ለማስተናገድ ተዘጋጅተን እየጠበቅን ነው ብላለች። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር መልካሙ አየለ እንዳሉት፥ የሲዳማ የዘመን መለወጫ በዓል ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል። የከተማዋ የፖሊስ ኃይል ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት አስቀድሞ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀው፥ በዓሉን ለመታደም የሚመጡ እንግዶች በዓሉን በሰላም እንዲያከብሩ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ ለ24 ሰዓት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሲዳማ የዘመን መለወጫ ፊቼ ጫምባላላ በዓል ዛሬና ነገ በሀዋሳ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
Mar 27, 2025 16
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ ተፈራርመዋል። ስምምነቱ ኢንቨስትመንትን ለማነቃቃት የሚያስችል የሚዲያ አጋርነት እና የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ገጽታ ለማጠናከር ያለመ እንደሆነም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፥ ኮሚሽኑ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሽግግር በመምራት ሂደት ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የሀገሪቱን የኢንቨስትመንት እድሎች ማስተዋወቅ ቀዳሚ ስራው መሆኑን ተናግረዋል።   መንግስት ለኢንቨስትመንት ምቹ ምህዳር በመፍጠር በርካታ ተግባራትን ማከናወኑንም አስረድተዋል። እንዲሁም በተለያዩ ዘርፎች ወደ ሥራ የገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን የመደገፍ እና የመከታተል ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። እነዚህን ተግባራት በአግባቡ ለማስተዋወቅ የሚዲያ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፥ ስምምነቱ እምቅ አቅሞችን ለመጠቀም የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የኢንቨስትመንት መረጃዎችን በሙያዊ እውቀትና በጥራት ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም መሆኑን አንስተው ከአገልግሎቱ ጋር በመስራታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው ስምምነቱ የኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻነት ለማስፋት እንደ ትልቅ እድል የሚወሰድ ነው ብለዋል። አገልግሎቱ የኮሚሽኑ ህልሞች እውን እንዲሆኑ በዜናና ዜና ነክ የዘገባ ስራዎች የማስተዋወቅ ሚናውን እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ለዚህም የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድሎች፣ የተፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎችን እና እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ተደራሽ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
ባንኩ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ የፋይናንስ አገልግሎቶች ማቅረቡን ያጠናክራል- አቤ ሳኖ
Mar 27, 2025 38
አዲስ አበባ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የባንኩ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከማስተር ካርድ ጋር በመተባበር ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ ዓለም አቀፍ የዲጂታል ክፍያዎችን ማድረስ የሚያስችሉ ፕላስቲክ እና ቨርቹዋል ቅድመ ክፍያ ማስተር ካርዶችን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ ባንኩ የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት በዲጂታል ፋይናንስ ላይ ትኩረት ያደረጉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከዚህም መካከል አዳዲስ አስተማማኝ የፋይናንስ ዲጂታል ቅድመ ክፍያ አገልግሎቶችን ለደንበኞቹ ለማቅረብ እያከናወነ የሚገኘውን ተግባራትን አንስተዋል፡፡ ባንኩ ዛሬ ይፋ ያደረገው ዓለም አቀፍ ፕላስቲክ እና ቨርቹዋል ቅድመ ክፍያ ካርዶች አዳዲስ እና አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለደንበኞች ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል፡፡ ዲጂታል የቅድመ ክፍያ ካርዶች በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ነጋዴዎች ተቀባይነት ያላቸው መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፥ ክፍያ ካርዶች የባንኩን የላቀ የደህንነት እርምጃዎች የሚያሳዩ መሆኑንም ተናግረዋል። በቀጣይ ባንኩ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት ለመመለስ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ የዓለም አቀፍ ዲጂታል ክፍያዎችን ተደራሽ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የማስተር አፍሪካ ፕሬዝዳንት ማርክ ኤሊዮት በበኩላቸው፤ በንግድ ባንክ ይፋ የተደረገውን የቅድመ ክፍያ ዲጂታል ማስተር ካርድ በታዳጊ የአፍሪካ ገበያዎች ለማሳደግ ለያዘው ስትራቴጂ ቁልፍ ምዕራፍን እንደሚከፍት አስታውቀዋል። ከንግድ ባንክ ጋር በመሆን ኢትዮጵያውያን በዓለም አቀፍ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንዲሳተፉ የሚያስችላቸው አስተማማኝ ዲጂታል የክፍያ መፍትሄ መቅረቡ የሚያኮራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በቀጣይ ማስተር ካርድ ከባንኩ ጋር ዲጂታል ቴክኖሎጂን የማሳደግ ስራ ላይ በጋራ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
በማዕከሉ የሚሰለጥኑ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማላቅ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረጋል - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
Mar 27, 2025 34
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፡- በማዕከሉ የሚሰለጥኑ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማላቅ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ያደርጋል ሲሉ የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከ"ለነገዋ" የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡ በማዕከሉ የሚሰለጥኑ ሴቶችን ተጠቃሚነት ማላቅ ላይ ባተኮረው የውይይት መድረክ የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሂርጳሳ ጫላ እና ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኤልሻዳይ ክፍሌ ተገኝተዋል፡፡   ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በውይይቱ እንደገለጹት፤ በማዕከሉ የሚሰለጥኑ ሴቶች በሥራ ገበያው ላይ ተፈላጊ የሆነ ክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማላቅ ይሰራል፡፡ በክህሎት ልማትና ሥራ ዕድል ፈጠራ መስኩ ያሉ ዕድሎችን እንዲጠቀሙ ከማድረግ ባሻገር የማዕከሉ አቅም ቀጣይነት ባለው መልኩ እንዲያድግ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ያደርጋል ማለታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
በዞኑ የበጋ መስኖ ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መጥቷል
Mar 27, 2025 41
አምቦ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ሸዋ ዞን የበጋ መስኖ ልማት የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ ምምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡   በጽህፈት ቤቱ የአዝእርት ልማትና የእጽዋት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ደጀኔ ገመቹ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥ አርሶ አደሩ የዝናብ ወቅትን ጠብቆ ከማምረት ወጥቶ በበጋ መስኖ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት መስራቱን ተናግረዋል። አርሶ አደሩ በተለይም በበጋ መስኖ አትክልትን በማልማት ኢኮሚያዊ ተጠቃሚነቱን ከማሳደግ ባለፈ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝ መድረጉን ጠቅሰዋል። በዞኑ የከርሰ ምድርና የገፀ ምድር ውኃ ሀብትን በመጠቀም ዘንድሮ በበጋ መስኖ በመጀመሪያው ዙር 30ሺህ 164 ሄክታር መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት 3ሚሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡ ባህላዊና ዘመናዊ የመስኖ አውታሮችን በመጠቀም ጎመን፣ ሽንኩርት፣ ሰላጣ፣ ቲማቲም፣ ካሮት፣ ድንችና ስኳር ድንች መልማታቸውን አንስተዋል። በሁለተኛ ዙርም 9ሺህ 224 ሄክታር መሬት በማልማት 4 ሚሊዮን ኩንታል የአትክልት ምርት ለመሰብሰብ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡   በበጋ መስኖ ልማቱ ከተሰማሩት አርሶ አደሮች መካከል የቶኬ ኩታዬ ወረዳ ነዋሪ አቶ አለሙ ፈይሳ፤ የውሀ አማራጮችን በመጠቀም በመስኖ ያለሙትን ቀይ ሽንኩርትና ቲማቲም ለገበያ በማቅረብ ከ250ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ የአምቦ ወረዳ አርሶ አደር በቀለ መገርሳ በበኩላቸው በመጀሪያው ዙር በመስኖ ካለሙት የጓሮ አትክልት ሽያጭ 300ሺህ ብር ገቢ ማግኘታቸውን አስታውሰዋል። በሁለተኛ ዙርም የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን ማልማት መጀመራቸውን አክለዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ወጣቱ በሳል የሆነ የማኀበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን መከተል ይገባዋል - ወጣቶች
Mar 27, 2025 43
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፡- ወጣቱ በሳል የሆነ የማኀበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በመከተል እንደሚገባው ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ገለጹ። ማህበራዊ ሚዲያ የሰው ልጅን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ እንዲሁም አኗኗር ቀላል እያደረገው መጥቷል። በአዲስ አበባ ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚወጡ መረጃዎችን በሙሉ ከመውሰድ ይልቅ አጣርቶ መጠቀም ይገባል ይላሉ። ወጣት ህይወት አምባው እንዳለችው፤ አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የተለያየ ዓላማን በመያዝ ሀሰተኛ መረጃዎችን ሲያሰራጩ ይስተዋላል። በመሆኑም መረጃዎቹን ከመጠቀም በፊት ትክክለኛነታቸውን ማጣራት ይገባል ብላለች። ወጣት ህይወት በማህበራዊ ሚዲያ የሚለቀቁ መረጃዎች ምንጫቸው ከየት ነው? ትክክለኛነቱስ ምን ያህል ነው? የሚለውን ማጤን ይገባልም ስትል ትመክራለች። ወጣቶች ትክክለኛ መረጃዎችን ከትክክለኛ ምንጮች በመውሰድ ራሳችንን ከሀሰተኛ መረጃ ከመጠበቅ ባለፈ ለህዝቦች አብሮነት መስራት አለብን ብላለች። ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለምን ዓላማ ነው የምንጠቀመው የሚለውን ቆም ብለን ልናስብ ይገባል ያለው ደግሞ ወጣት ሃይለማሪያም ተሰማ ነው። የወጣቱ ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ብስለት የተሞላበት ሊሆን እንደሚገባና ሚዲያውን ለበጎ ነገር መጠቀም ይገባል ብሏል። በማህበራዊ ሚዲያ በርካታ ተከታዮችን ማፍራት መቻሉን የጠቀሰው ወጣት በረከት ከበደ በበኩሉ በማህበራዊ ሚዲያው የሚያስተላልፈውን መልዕክት ለሀገርና ለሕዝብ ምን ያህል ይጠቅማል የሚለውን የመመዘን ልምድ እንዳለው ገልጿል። በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ያለውን ልምድ ለወጣቶች በማካፈል የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑንም ነው የጠቆመው። ወጣት መንበረ መልኬ በበኩሉ ወጣቱ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለሀገር የሚጠቅም ገንቢ ሚና እንዲጫወት ግንዛቤን የማስፋት ሥራ ሊጠናከር ይገባል ብሏል። ለዚህም ባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን መስጠት ላይ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ በመጠቆም።
ሴቶች በሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፍ የግንባር ቀደምትነት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል
Mar 26, 2025 62
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፦ ሴቶች በሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፍ የግንባር ቀደምትነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ ሴቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማህበር (SEWIST) 6ኛ ዓመታዊ ጉባኤ ተካሂዷል።   ጉባኤው የተካሄደው "የወደፊቱን የሚመሩ ሴቶች፤ የሴት ተመራማሪዎችን በሳይንስ፣በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ማብቃት" በሚል መሪ ሀሳብ ነው። የማህበሩ ጉባዔ ሴቶችን በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ ፣ፈጠራና ምርምር እድገት ያላቸው ሚና፣ ያሉ እድሎች እና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ሴቶች በሳይንሳዊ ግኝቶች፣ በቴክኖሎጂ እድገት እና በፈጠራ መፍትሄዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊወጡ ይገባል። በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ /STEM/ ዘርፎች የሴት ምሁራን ሚና ወሳኝ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መፍትሄ ለማምጣት ሴቶችን ያሳተፈ ስራ ማከናወን እንደሚያስፈልግም አመልክተዋል። ማህበሩ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና የምርምር ተቋማት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሴቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማህበር ፕሬዝዳንት ሄለን ንጉሤ(ዶ/ር ) ኢትዮጵያ በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን በርካታ ስራዎች እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል። በዘርፎቹ የተሟላ ውጤት ለማምጣት የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግና ሒሳብ /STEM/ ዘርፎች ያላቸውን አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሴቶች በሳይንስና ቴክኖሎጂ ማህበር በ2014 ዓ.ም የተቋቋመ እና በሳይንስ ፣ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ሚኒስቴሩ በመረጃው አመልክቷል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታ ለአፍሪካ ሀገራት ትምህርት ይሆናል
Mar 26, 2025 84
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሀገራት ትምህርት የሚሆን የዲጂታል ኢኮኖሚና መሰረተ ልማት እየገነባች መሆኑን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የፈጠራና ቴክኖሎጂ ክፍል ኃላፊ ማክታር ሳክ(ዶ/ር) ገልጸዋል። ኃላፊው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአፍሪካ ሀገራት ጠንካራ የዲጂታል ፖሊሲ በመዘርጋት የከተማና ገጠር የቴክኖሎጂ ትስስርን በማስፋፋት በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቅባቸዋል። ኢትዮጵያ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ በሰጠችው ትኩረት በስራ ዕድል ፈጠራና በኢንቨስትመንት ፍሰት እመርታዊ ለውጥ እያስመዘገበች እንደምትገኝ ገልጸዋል። መንግሥት ለዲጂታላይዜሽን በሰጠው ትኩረት የኢንተርኔት መሰረተ ልማት ተደራሽነት በሀገሪቱ በእጅጉ መስፋፋቱን አድንቀዋል። ጠንካራ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የአሰራር ማዕቀፍ በማዘጋጀት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነትን ማቀላጠፍ እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል። የበይነ መረብ ግንኙነት ዕድገትም ለአህጉሪቱ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሳካት ወሳኝ በመሆኑ ለአፍሪካውያን ተመጣጣኝ አገልግሎት ማቅረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ በዲጂታል መሰረተ ልማትና ኢኮኖሚ ግንባታ ለአፍሪካውያን ትምህርት የሚሆን ስኬት እያስመዘገበች ነው ብለዋል።   የቴክኖሎጂ ንግድ ልማትና ግብይት ባለሙያ የሆኑት ሰርጌይ ጋስፓርያን በበኩላቸው፤ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት የሀገር ውስጥ ገቢ የመሰብሰብ አቅምን ለማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ዲጂታላይዜሽን የፋይናንስ አስተዳደርንና የታክስ የመሰብሰብ ሂደትን በማቀላጠፍ ግልጽነት ያለው የገቢና ወጪ ሥርዓት ለመፍጠር ጉልህ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። ኢትዮጵያም የአምስት ዓመታት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስትራቴጂ በመቅረጽ ባለፉት ዓመታት ያከናወነቻቸው ተግባራት የሚደነቁ ናቸው ብለዋል። በቀጣይም ከዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ምርትና አገልግሎት ሰጪዎች ጋር በመተባበር የዕውቀትና ክህሎት ሽግግር ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም አንስተዋል። ኢትዮጵያ የመንግስትን የመፈጸም አቅም በማሳደግ ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገት በመፍጠር አስደናቂ የልማት እንቅስቃሴ እያደረገች መሆኗንም ጠቅሰዋል።
ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ በዲጂታላይዜሽን እና በቴክኖሎጂ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለዓለም ማስተዋወቅና ትስስር መፍጠር ያስችላል
Mar 26, 2025 74
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፡- ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና በቴክኖሎጂ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለዓለም የሚያስተዋውቅ እና ትስስር የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል፡፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) በጋራ የሚያዘጋጁትን ኤክስፖ በተመለከተ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ እንደገለጹት፤ ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 ከግንቦት 8 ቀን ጀምሮ ለሶስት ቀናት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል፡፡   ኤክስፖው ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ያስመዘገበቻቸው ስኬቶችን እና በዲጂታል ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለዓለም ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ኤክስፖው የሳይበር ደህንነት፣ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የፋይናንስ ደህንነት፣ ስማርት ሲቲ እና የቴክኖሎጂ ትምህርት ትኩረት የሚያደርግባቸው መስኮች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም ከ10 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች፣ ከ100 በላይ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እንዲሁም ከ50 በላይ ስታርታፖች ምርትና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት መድረክ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ ኤክስፖው ከ20 በላይ ጥናቶች፣ የፓናል ውይይቶች እንዲሁም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሮቦቲክስ ውድድሮች የሚካሄዱበት መድረክ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ ስለሆነም በኢትዮጵያ የተሰናዳው ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በተሳታፊም ሆነ በትኩረት መስኩ የምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የቴክኖሎጂ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኤክስፖው ከአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎትና በሌሎች የቴክኖሎጂ መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶቿን ለዓለም የምታስተዋውቅበት፣ ከሌሎች ልምድ የምትቀስምበትና ትስስር የምትፈጥርበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ከቅንጦት ይልቅ በሽታን በመከላከል፣ ትምህርትን በማስፋፋትና ድህነትን በመቀነስ ለሰው ልጅ መሰረታዊ ጉዳይ እየሆነ መምጣቱን አንስተዋል፡፡ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ታዳጊ ሀገራት የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ከድህነት ለመውጣት ለሚደረገው ጥረት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል፡፡ በተለይም የግሉ የቴክኖሎጂ ተዋንያን በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ በሰው ሰራሽ አስተውሎትና በሌሎች የቴክኖሎጂ ዘርፎች ልምድ የሚለዋወጡበትን አውድ ይፈጠራል ብለዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ ጅቡቲን በሰፊ የግብ ልዩነት በማሸነፍ በማጣሪያው የመጀመሪያ ድሏን አስመዝግባለች
Mar 25, 2025 125
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ስድስተኛ የምድብ ጨዋታ ጅቡቲን 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች። ማምሻውን በሞሮኮ ኤል ጀዲዳ ከተማ በሚገኘው ኤል አብዲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቡበከር ናስር በጨዋታ ሁለት፣ በፍጹም ቅጣት አንድ ጎል በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። በተመሳሳይ በረከት ደስታ ሁለት በጨዋታ፣ አንድ በፍጹም ቅጣት በማግባት ሀትሪክ መስራት ችሏል። ሳሙኤል አኪንቢኑ ለጅቡቲ ብቸኛውን ግብ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከተሎ በምድብ አንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያው የመጀመሪያ ድሏን አስመዝግባለች። በምድቡ በስድስት ነጥብ ደረጃዋን ከ5ኛ ወደ 4ኛ አሻሽላለች። በማጣሪያው አምስተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ጅቡቲ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን 6ኛ ደረጃን ይዛለች። በተያያዘም በዚሁ ምድብ ዛሬ በተደረገው ጨዋታ ቡርኪናፋሶ ከሜዳዋ ውጪ 2 ለ 1 አሸንፋለች። ውጤቱን ተከትሎ ቡርኪናፋሶ ነጥቧን ወደ 11 ከፍ በማድረግ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ምድቡን በ13 ነጥብ የምትመራው ግብጽ ነገ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በካይሮ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ሴራሊዮንን ታስተናግዳለች። ሴራሊዮን በ8 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የኢትዮጵያ እና ጅቡቲ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ
Mar 24, 2025 97
አዲስ አበባ፤መጋቢት 15/2017 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በ23ኛ የፊፋ ዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ዞን ማጣሪያ ስድስተኛ ጨዋታውን ዛሬ ከጅቡቲ ጋር ያደርጋል። የሁለቱ ሀገራት ጨዋታ ከሌሊቱ 6 ሰዓት ላይ በሞሮኮ ኤል ጄዲካ ከተማ በሚገኘው ኤል አብዲ ስታዲየም ይካሄዳል። ዋልያዎቹ ከቀናት በፊት ከግብጽ ጋር ባደረጉት አምስተኛ የምድብ ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፈዋል። በምድብ አንድ ሶስት ነጥብ ይዘው አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ጅቡቲ ቡርኪናፋሶ ጋር ባደረገችው የማጣሪያ መርሃ ግብር የ4 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዳለች። ቡድኑ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ለጨዋታው የመጨረሻ ልምምዱን ትናንት ማድረጉን ኢዜአ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘው መረጃ ያመለክታል። 23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እ.አ.አ በ2026 በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጣምራ አዘጋጅነት ይካሄዳል። በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ 48 ሀገራት ይሳተፋሉ። በዓለም ዋንጫ ለመሳተፍ 54 የአፍሪካ ሀገራት በዘጠኝ ምድብ ተከፍለው የማጣሪያ ጨዋታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። አፍሪካ በዓለም ዋንጫው 9 ሀገራት በቀጥታ ታሳትፋለች። ይህም ከዚህ ቀደም ከነበረው የ5 ሀገራት ተሳትፎ እድገት አሳይቷል። አንድ የአፍሪካ ቡድን በሌሎች አህጉራት ከሚገኙ ሀገራት ጋር በሚደረግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ካሸነፈ አህጉሪቷን የሚወክል 10ኛ ሀገር ይሆናል።
አካባቢ ጥበቃ
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለሀገር በቀል የአየር ንብረት ለውጥ መከላከያ ኢኒሼቲቮች ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ አለበት - ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር)
Mar 27, 2025 83
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እየተገበሯቸው ላሉ ሀገር በቀል ኢኒሼቲቮች ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርግ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ።   በጀርመን በርሊን ከተማ እየተካሄደ ያለው የ2025 የፒተርስበርግ የአየር ንብረት ለውጥ ምክክር እንደቀጠለ ነው። በመድረኩ ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ተጽእኖ ለመቀነስ እና ለመከላከል እየወሰደቻቸው ያሉ ሀገር በቀል እርምጃዎችን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአረንጓዴ አሻራ ስኬቶች በምክክሩ ላይ አድናቆት የተቸረው ሲሆን ኢኒሼቲቩ ሊደገፍ እና ሌሎችም ሀገራት ሊተገብሩት እንደሚገባ ተገልጿል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የደን ሽፋን በኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረበት እአአ 2019 ከነበረበት በ6 በመቶ ጨምሮ እአአ በ2023 የደን ሽፋኑ 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል፡፡   ኢኒሼቲቩ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ማህበረሰቦችን ኑሮ እና የአኗኗር ዘይቤ እንዲለወጥ አስተዋጽኦ ማድረጉንም ገልጸዋል። የፍራፍሬ እና የጥምር ደን ችግኞችን በመትከል አርሶ አደሮች አቮካዶን ጨምሮ የተለያዩ መርቶችን ኤክስፖርት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አመልክተዋል። መሰል ሀገር በቀል የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተሞክሮዎች ተጽእኖውን ከመቀነስ ባለፈ የዜጎችን የኢኮኖሚ ፍላጎት መመለስ የሚያስችል ነው ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና እያጋጠማቸው ላሉ ሀገራት ችግሩን ለመከላከል እየወሰዱት ላለው እርምጃ ፋይናንስን ጨምሮ ሌሎች ድጋፎችን እንዲያደርጉም ሚኒስትሯ ጥሪ አቅርበዋል።   በተጨማሪም ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ከምክክሩ ጎን ለጎን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ልዩ አማካሪ ሴልዊን ሀርት ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም የሶስተኛው ዙር ብሄራዊ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅድን ጨምሮ የአየር ንብረት ለውጥ ፖሊሲ እቅድ ሂደት ላይ በትብብር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የማጣጣሚያ እቅዱን ከቀናት በፊት ይፋ ያደረገች ሲሆን እቅዱን በብራዚል ከሚካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ(ኮፕ 30) በፊት ለማስገባት እየሰራች መሆኑም ተጠቁሟል። በውይይቱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ኢትዮጵያ እ.አ.አ ሴፕቴምበር 2025 በምታዘጋጀው ሁለተኛ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ላይ መሳታፍ የሚችሉበትን መንገድ በጋራ ለማመቻቸት ከመግባባት ላይ መደረሱም ተገልጿል። በተያያዘም ሚኒስትሯ ብሄራዊ የአየር ንብረት ለውጥ ማማጣሚያ እቅድ የድጋፍ ቡድን ዓለም አቀፍ ዳይሬክተር ፓብሎ ቪዬራ ጋርም ተወያይተዋል። ዳይሬክተሩ የኢትዮጵያ የብሄራዊ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ ዕቅድ እና ትግበራ ውጤታማ እንዲሆንና ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ በስኬት እንድታዘጋጅ ድጋፍ እንደሚያደርግ መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል። የ2025 የፒተርስበርግ የአየር ንብረት ለውጥ ምክክር በጀርመን እና ብራዚል መንግስታት የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ነው።
ኢትዮጵያ ዩኤን ሀቢታት ለከተማ ኑሮ እና መሰረተ ልማትን ማሻሻያ ኢኒሼቲቮች ድጋፍ እንዲያደርግ ጠየቀች
Mar 26, 2025 58
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ሰፈራ መርሃ-ግብር (ዩኤን ሀቢታት) የከተማ ኑሮ እና መሰረተ ልማትን የሚያሻሽሉ ኢኒሼቲቮችን እንዲደግፍ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን ጥሪ አቀረቡ። በከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን የተመራ ከፍተኛ የመንግስት ልዑክ በኬንያ እየተካሄደ ባለው የመጀመሪያው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ሰፈራ መርሃ-ግብር (ዩኤን ሀቢታት) የስራ አስፈጻሚ ቦርድ ስብስባ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። የቦርድ ስብስባው ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። በስብሰባው ላይ ዩኤን ሀቢታት በኢትዮጵያ እና በሌሎች ሀገራት እያከናወናቸው ያሉ ስራዎችን አስመልክቶ ሪፖርት አቅርቧል። በሪፖርቱ ኢትዮጵያ በከተማ ልማት እያከናወነች ያለው ስራ ከፍተኛ አድናቆት ማግኘቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያም የከተማ ልማት የስኬት ተሞክሮዎቿን አቅርባለች። የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን ኢትዮጵያ በዩኤን ሀቢታት የሚደገፉ እንዲሁም ከብሄራዊ የከተማ ልማት ፖሊሳዊ እና የ10 ዓመት የልማት እቅዷ ጋር የተናበቡ ፕሮጀክቶቿን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። ዩኤን ሀቢታት የከተማ ኑሮ ሁኔታ እና መሰረተ ልማት ማሻሻያ ኢኒሺዬቲቮችን በተጠናከረ መልኩ እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል። በተጨማሪም ሚኒስትር ዴኤታው ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2029 ለመተግበር ያዘጋጀው ረቂቅ የስትራቴጂክ ፕላን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን የቤቶች አቅርቦት ፈተናዎችን በግልጽ ያስቀመጠ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የማይበገር የከተማ የቤት ልማት አሰራርን ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነችም ገልጸዋል።  
ረቂቅ አዋጁ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ሥርዓትን የሚያዘምን ነው
Mar 26, 2025 54
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፦ ረቂቅ አዋጁ የተቀናጀና ዘላቂነት ያለው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ሥርዓትን ለማዘመን እንደሚያግዝ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ ተናገሩ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 1/2017 ዓ.ም ባካሄደው 10ኛ መደበኛ ስብሰባው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ የማሻሻያ ረቂቅ ላይ ተወያይቶ ለውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና የአካባቢ ልማት እንዲሁም ለከተማ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴዎች መምራቱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም ሁለቱ ቋሚ ኮሚቴዎች እና የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በረቂቅ አዋጁ ላይ ዛሬ ይፋዊ የሕዝብ ውይይት መድረክ አካሂደዋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ አረንጓዴ፣ ውብና ፅዱ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍና ለአካባቢ ምቹ መደላድል የሚፈጥር ሕግ አስፈላጊ እንደሆነም ገልጸዋል። ነባሩ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ አዋጅ ቁጥር 513/1999 አሁን ካለው የሀገሪቱ ዕድገት አንጻር ክፍተቶች ያሉበት በመሆኑ ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። ከከተሞች መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሚመነጨው የቆሻሻ መጠን እየጨመረ በመምጣቱ በነባሩ አዋጅ መምራት ባለመቻሉም አዲስ አዋጅ ማዘጋጀት ማስፈለጉን ጠቁመዋል። አግባብነት የሌለው የቆሻሻ አወጋገድ ለአፈር፣ ለውሃ፣ ለአካባቢ እና ለአየር ንብረት ብክለት እንደሚያጋልጥ ጠቅሰው፥ ቆሻሻውን ከምንጩ ለመቀነስና የአያያዝና የአወጋገድ ስርዓቱን ማሻሻል አስፈላጊ እንደሆነም አንስተዋል። ደረቅ ቆሻሻ በአካባቢ ሥነ-ምህዳር እና በሰዎች ደኅንነትና ጤና ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሆኑ ይህን በሕግ ምላሽ ለመስጠት አዋጁ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል ፕላስቲክ ማምረት፣ ለገበያ ማቅረብ፣ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት፣ መሸጥ፣ ማከማቸት ወይም መጠቀም በረቂቅ አዋጁ የተከለከለ መሆኑን ተናግረዋል። የተሻሻለው ረቂቅ አዋጅ ሲተገበር በሀገሪቱ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ስርዓት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንደሚያመጣም ገልጸዋል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የተቋማት ተወካዮች በበኩላቸው የአካባቢ ጥበቃና ቆሻሻን በአግባቡ ማስወገድ የሁሉም ድርሻ በመሆኑ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ፕላስቲክና ጎማ አምራቾች ማህበር ፕሬዝዳንት ምንተስኖት ለማ የአካባቢ ጥበቃ የሁላችን ጉዳይ ነው፤ ነገር ግን አንዳንድ በረቂቅ አዋጁ የተካተቱ ድንጋጌዎች በአምራቾች ላይ ጫና የማያሳድሩ እንዲሆኑ ጠይቀዋል። የውሃ፣መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና የአካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፈትያ አህመድ ረቂቅ አዋጁ ለአካባቢ ጥበቃ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ ከህዝብ የቀረቡ ጥያቄዎችና ሀሳቦች ለረቂቅ አዋጁ ተጨማሪ ግብዓት ይሆናሉ ብለዋል። የከተማ፣ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ እሸቱ ተመስገን(ዶ/ር) በበኩላቸው ሀገር ያለችበትን የኢኮኖሚ እድገትና የከተሞች መስፋፋት እንዲሁም የማኅበረሰብ ዕድገት ማዕከል ያደረገ የቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በረቂቅ አዋጁ ላይ አስፈላጊ ግብዓቶችን በመሰብሰብ ጠንካራ አዋጅ ማዘጋጀት ይቻል ዘንድ ይፋዊ የሕዝብ ውይይት መድረኩ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በሰሜን ወሎ ዞን የበጋ ወቅት በ26ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ የማከናወን ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Mar 26, 2025 63
ወልዲያ፤መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፡-በሰሜን ወሎ ዞን የበጋ ወቅት በ26ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ የማከናወን ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ምክትል ኃላፊ አቶ ቦጋለ ሰጤ፤ በዞኑ በዘንድሮ የበጋ ወቅት 26ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህም በ665 ተፋሰሶች ላይ እየተከናወነ የሚገኘው የልማት ሥራው እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ 90 በመቶውን በውጤታማነት ማጠናቀቅ መቻሉን ገልጸዋል። ቀሪው ተግባር በቀጣይ 15 ቀናት ውስጥ ለማጠናቀቅ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመው፤የተራራና የማሳ ላይ እርከንና የቦረቦር መሬትን ማዳን ላይ በማተኮር ተግባሩ ተከናውኗል ብለዋል። በልማት ሥራው በድግግሞሽ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ህዝብ በመሳተፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ ከአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊየን ብር በላይ ግምት ያለው መሆኑን አስረድተዋል። በጉባላፍቶ ወረዳ የዝርጋ ቀበሌ አርሶ አደር ወርቁ ጽጌ በሰጡት አስተያየት፤ባለፋት ዓመታት በሰራናቸው ስራዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ስላገኘን ዘንድሮ በቁርጠኝነት እንድንሰራ አነሳስቶናል ብለዋል። ቀድሞ ከለማው ተፋሰስ የእንስሳት መኖና ለቤት መስሪያ እንጨት በነጻ በማግኘታቸው ተጠቃሚ እንደሆኑ አውስተው፤ ዘንድሮ ግንባር ቀደም በመሆን በልማቱ መሳተፋቸውን አስታውቀዋል። የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ሥራ የአካባቢያችን ተራራዎች ልምላሜና ቦረቦሮችም ተስተካክለው ወደ ቀድሞ ይዞታቸው እየተመለሱ መሆኑን የገለጹት በግዳን ወረዳ የእየላ ቀበሌ ነዋሪው አቶ አገኘሁ መኩሪያ ናቸው። የተራሮች በደን መሸፈን ምንጮች እንዲጎለብቱና የእርሻ ማሳንም እርጥበት በመያዝ ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ጎመንና ሠላጣ በማልማት መጠቀም እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነትን በማጽደቅ 48 ሃገራት ቁርጠኝነታቸውን አሳይተዋል
Mar 25, 2025 74
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያን ጨምሮ እስካሁን 48 ሀገራት የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነትን በማጽደቅ ለትግበራው ቁርጠኛነታቸውን ማሳየታቸውን የአህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣናው ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ ገለጹ። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና በአፍሪካ አጀንዳ 2063 የልማት ማዕቀፍ ከተያዙ ግዙፍ አህጉራዊ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ሲሆን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ስር ከሰደደ ድህነት እንደሚያላቅቅ ይጠበቃል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት መሪዎች አህጉራዊ የነጻ ንግድ ቀጣና መመስረቻ ስምምነትን እ.ኤ.አ. በ2018 በሩዋንዳ ዋና ከተማ ኪጋሊ መፈረማቸው ይታወቃል። ኢትዮጵያም ስምምነቱን በወቅቱ ከመፈረም ባለፈ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኩል መጋቢት 12/2011 ዓ.ም አፅድቃለች። ዋና ጸሐፊው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ አህጉራዊ የነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነቱን 48 የአህጉሪቱ አባል ሀገራት አጽድቀውታል። እነዚህ ሀገራት ስምምነቱን ለመተግበር ያላቸውን ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት ማሳየታቸውን ጠቅሰው፤ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ ጠንካራ የህግ ማዕቀፎች እያዘጋጁ ነው ብለዋል። ከዚህም ባለፈ 19 አባል ሀገራት የቀረጥ መርሃ ግብር በማውጣት የንግድ ግብይት ለመፍጠር መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። አክለውም የአነስተኛና መካከለኛ አርሶ አደሮችን ምርት በማሰባሰብ አህጉራዊ የንግድ ትስስርን የሚያጠናክሩ ድርጅቶችን ለማቋቋም ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የንግድ ድርጅቶችን ለማቋቋም በሚደረገው ጥረትም የአፍሪ-ኢግዚም ባንክ ለነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነቱ የ750 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑንም አስረድተዋል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ ውህደትና ዕድገት በማረጋገጥ የህዝቧን ተጠቃሚነት ማጎልበት የህልውና ጉዳይ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የቀድሞ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ዬሚ ኦሲንባጆ ናቸው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነትን በጠንካራ የፖለቲካ አመራር መተግበር የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ውህደት ለማፋጠን ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም ተናግረዋል። ከአህጉራዊ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክት መካከል አንዱ የሆነው ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነቱ፤ የአፍሪካን የወደፊት የኢኮኖሚ እጣ ፋንታ የሚወስን መሆኑንም ተናግረዋል። የአፍሪካ የኢኮኖሚ ውህደትና ዕድገት የህዝቦችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የህልውና ጉዳይ ተደርጎ መታየት እንዳለበት ጠቅሰው፤ ለስኬቱም ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው ብለዋል። የአፍሪካን አህጉራዊ ውህደት ራዕይን እውን ለማድረግ እ.ኤ.አ በ1963 ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት መቋቋም ጀምሮ የተለያዩ ጥረቶች ተደርገዋል። ለአብነትም የአፍሪካ መሪዎች እ.አ.አ በ2012 በአዲስ አበባ በተካሄደው የህብረቱ 18ኛ መደበኛ ጉባኤ አህጉራዊ የነጻ ንግድ ቀጣና እንዲመሰረት ውሳኔ ማሳለፋቸው ይታወቃል። ይህንን ተከትሎም እ.ኤ.አ በ2015 ድርድሩን በይፋ በመጀመር በ2018 አህጉራዊ የነጻ ንግድ ቀጣና መመስረቻ ስምምነቱ በይፋ ተፈርሟል። የአፍሪካ የነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነት 55 የአፍሪካ ሀገሮችን በአንድነት ያካተተ የነጻ ንግድ ስርዓት የፈጠረ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነ ስምምነት ነው፡፡ የአፍሪካ ሀገራት በአብዛኛው እቃዎች ላይ በሂደት ታሪፍን ለማስወገድ፣ የአገልግሎት ንግድን በሂደት ክፍት ለማድረግ እና የንግድ መሰናክሎችን ለማስወገድ የተስማሙበትም ነው፡፡
ኢጋድ በደቡብ ሱዳን ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን በቁርጠኝነት ይሰራል - ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር)
Mar 14, 2025 166
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) በደቡብ ሱዳን ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ የተቋሙ ዋና ጸሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) ገለጹ። ዋና ፀሐፊው ከወቅቱ የኢጋድ ሊቀ መንበር እና የጅቡቲ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ የደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ከትናንት በስቲያ በተካሄደው 43ኛው የኢጋድ አስቸኳይ የመሪዎች ጉባኤ ውጤቶች ላይ ያተኮረ ነበር።   ዋና ጸሀፊው ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) በውይይቱ በጉባዔው ላይ የተላለፉ ውሳኔዎች ተግባራዊነት እና ኢጋድ ቀጣናዊ ፈተናዎችን ለመፍታት ያለው ቁርጠኝነት ላይ ከሊቀመንበሩ ጋር ሀሳቦች እንደተለዋወጡ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል። ኢጋድ በደቡብ ሱዳን ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በሙሉ ቁርጠኝነት እንደሚሰራ አመልክተዋል። አስቸኳይ ጉባኤውን ተከትሎ የደቡብ ሱዳን ኃይሎች አለመግባባቶችን በውይይት እና በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንዲፈቱ ኢጋድ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል።
ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ መሻሻል አለባቸው
Feb 12, 2025 525
አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ መሻሻል እንዳለባቸው በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ። 46ኛው የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የስራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ እየተካሔደ ይገኛል። በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ በዚህ ወቅት፤ አፍሪካውያን የተፈጥሮ ሀብታቸውን በአግባቡ መጠቀም አልቻሉም ብለዋል። አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የምታሳድረው ተፅዕኖ ጥቂት ቢሆንም የጉዳቱ ገፈት ቀማሽ መሆኗን ገልጸዋል። በመሆኑም የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የአፍሪካን ጥቅም በሚያስከብር መልኩ ሪፎርም መደረግ አለባቸው ብለዋል። የዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት በመሰረታዊነት መቀየር እንዳለበትም ገልጸዋል። አፍሪካውያን አህጉራዊ ሀብታቸውን እሴት ጨምረው መጠቀም እንዲችሉ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በአህጉሪቱ ጥሬ ምርትን ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ በምርቶች ላይ እሴትን ጨምሮ የመላክ አቅምን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል። አፍሪካውያን ለደረሰባቸው ግፍና በደል ተገቢ የፍትሕ ካሳ ሊያገኙ እንደሚገባም ገልጸዋል። ይህ ችግር የዓለም የንግድ ስርዓትን በማዛባት የአፍሪካውያንን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት በእጅጉ የጎዳ መሆኑን ተናግረዋል። አፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ላይ ያላት አሉታዊ ተፅዕኖ ውስን ቢሆንም የጉዳቱ ሰለባ ከመሆን አልዳነችም ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ አፍሪካን የአህጉራዊ ጥቅል ምርቷን አምስት በመቶ እንደሚያሳጣት በመጥቀስ፣ በዓለም ዙሪያ ለኢንቨስትመንት ከሚመደበው ሀብት የአፍሪካ ሁለት በመቶ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ይሄ የአፍሪካን ጥቅም የሚጎዳ ኢፍትሃዊነት በቃህ ሊባል ይገባል ብለዋል። ለዚህ ደግሞ የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት መሰረታዊ ሪፎርም ሊደረግባቸው እንደሚገባ ገልጸዋል።  
ሐተታዎች
አፊኒ ሶንጎ
Mar 19, 2025 111
በሀብታሙ መኮንን (ከሀዋሳ ኢዜአ) ኢትዮጵያ ሠላሟ ፀንቶ፣ ህዝቦቿም ወንድማማችነትና አብሮነታቸው ደምቆ እንድትቀጥል የሚያስችሏት የበርካታ ባህላዊ እሴቶች ባለቤት ናት። ለጠብ የሚጋበዙትን በእርጥብ ቄጤማ አቀዝቅዘው የሚያበርዱ፣ በቂም ቁርሾ ተነሳስተው በነፍስ የሚፈላለጉትን በባህል እሴት አስረው በፍቅር የሚያዋድዱ የበርካታ ማንነቶች ባለቤት ናት - ሀገራች ኢትዮጵያ። የሲዳማ “አፊኒ”፣ የራያ “ዘወልድ”፣ የኦሮሞ “ጃርሱማ”፣ የጋሞ “ዱቡሻ”፣ የጌዴኦ “ጎንዶሮ”፣ የጉራጌ “የጆካ”፣ የካፋ “ቃብትኖ” እና በየአካባቢው ያሉ ሌሎች ሀገር በቀል የእርቅና የሠላም እሴቶች ሰላምን በማውረድ ለዘመናት ተከባብረው የኖሩ ህዝቦችን የፈጠሩ የጋራ ማንነት ውጤቶች ናቸው። “አፊኒ” የተሰኘው ባህላዊ የዳኝነት ሥርዐት የሲዳማ ህዝብ ከጥንት ጀምሮ የተጣላን ሲያስታርቅበት፣ "በደሌን ስሙልኝ" ብሎ ለቀረበ አቤቱታ አቅራቢ ደግሞ ጉዳዩን መርምሮና “ሀላሌ”ን ገልጦ በዳይ እንዲክስ፤ ተበዳይ ደግሞ እንዲካስ የሚያደርግ ነው። ችግሩን በዕርቀ ሠላም ቋጭቶ፣ ተመራርቆና “ማጋኖ”ን አመስግኖ የሚኖርበት ቱባ እሴት ነው ማለትም ይቻላል፡፡ በሲዳማዎች ዘንድ እንዲህ ይነገራል “ጥንት ማጋኖና የሰው ልጆች አብረው ይኖሩ ነበር። ከጊዜያት በኋላም ማጋኖ የሰው ልጆችን ምድር ላይ ትቶ ወደ ሰማይ የሚሄድበት ጊዜ ደረሰ። በዚህን ጊዜ ሽማግሌዎች ማጋኖን "እኛን ለማን ትተኸን ትሄዳለህ" ሲሉ ጠየቁት። ማጋኖም "ለእናንተ ሀላሌን እተውላችኋለሁ" ብሎ ሀላሌን በሽማግሌዎች እጅ አኑሮ ሄደ ይባላል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በሲዳማ ሰማይ ስር ሁሌም “ሀላሌ” ባለበት “ማጋኖ” በመንፈሱ አለ ተብሎ ይታሰባል። “ሀላሌ” በሲዳማዎችና በ“ማጋኖ” መካከል ያለ የቃልኪዳን ውል ነው። በሲዳማዎች ዘንድ “ሀላሌ” የሁሉ ንጉስና ፈጣሪ ከሆነው “ማጋኖ” የተበረከተ እልፎች የሚገዙለት ረቂቅ ንጉስ ተደርጎም ይወሰዳል። መናገሻ አደባባዩ ደግሞ “አፊኒ ሶንጎ” ይባላል።   አንድ የሲዳማ ተወላጅ “ማጋኑ ሀላሌቲ” ካለ ትርጉሙ የፈጣሪ ዕውነት እንደማለት ሲሆን አንድም ትልቁን መሀላ እየማለ፤ አንድም ደግሞ የእውነት ምንጭ ፈጣሪ መሆኑን እየገለጸ ነው፡፡ በዘመነኛው ዓለም የዕውነት ትርጓሜው ብዙ፤ ፍልስፍናውም ውስብስብ ነው። ይህ ዓለም አንዳንዴም "ዕውነት አንፃራዊ ነው" የሚል ፍልስፍናዊ ድምዳሜ ይሰጣል። ሰዎች ያመኑበት ሀሳብ ለእነርሱ እውነት ነው፡፡ በአንፃሩ ይህ ሀሳብ በሌሎች ዘንድ ላይታመንበትና እውነት ላይሆን ይችላል። በአራቱም ጫፍ ላሉ ሲዳማዎች ግን ዕውነት ማለት “ሀላሌ” ነው፡፡ እንዳይጨመርበት ምሉዕ፤ እንዳይቀነስበት ልክ የሆነ፤ ረቂቅ ሆኖ የሚጨበጥ አንድ ቃል ሆኖ ሺህ ቃላትን የሚረታ የፈጣሪ እውነት። “ሀላሌ” ከነ ሙሉ ክብሩ የሚነግስበት የ“አፊኒ” ሥርዐት የሚካሄድበት የሸንጎ አደባባይ ደግሞ “አፊኒ ሶንጎ” ይባላል። “አፊኒ” የሲዳማ ህዝብ ያዳበረው የሠላምና የአብሮነት እሴት የሚታይበት ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓት ነው። እንደ ሀገር እየተተገበሩ ካሉ የሪፎርም ሥራዎች መካከል ባህላዊ የዕርቅና የዳኝነት ሥርዐቶችን ማጎልበትና ተሞክሮዎችን በማስፋት ህብረተሰቡ በመደበኛነት እንዲገለገልባቸው ማድረግ የሚጠቀስ ነው። የ“አፊኒ” ባህላዊ የዳኝነት ሥርአትን ጠብቆ ያቆየውና ባለቤት የሆነው የሲዳማ ህዝብ በስፋትና በላቀ ደረጃ መጠቀም እንዲችል የሲዳማ ክልል መንግስት ሥርአቱ በሕግ ማዕቀፍ እንዲደገፍ ከማድረግ ጀምሮ የተለያዩ ተጨባጭ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የክልሉ ምክር ቤት የ“አፊኒ ሶንጎ” ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 42/2016ን በማፅደቅ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዐቱ ሕጋዊ ሰውነት ኖሮት ህዝቡ መገልገል እንዲችል መሰረት ጥሏል፡፡ ይህን አዋጅ መሰረት በማድረግ የሚመለከታቸው የክልል አካላት ከፌዴራል አካላት ጋር በመሆን የቅድመ ዝግጅትና የአደረጃጀት ሥራዎችን ሲያከናውኑ ቆይተዋል፡፡ በዚህም መሠረት የ“የአፊኒ ሶንጎ” ማቋቋሚያ እና እውቅና መስጫ መርሀ ግብር ባለፈው የካቲት ወር በተለያዩ ወረዳዎች የተካሄደ ሲሆን ባህላዊ የዳኝነት ሥርዐቱ በሁሉም ወረዳዎችና ቀበሌዎች በመደበኛነት አገልግሎት እንዲሰጥም ይፋዊ የማስጀመሪያ መርሀግብርም ተካሂዷል ፡፡   የፍትሕ ሚኒስቴር ላለፈው አንድ ዓመት ተኩል ተግባራዊ እያደረገ በቆየው የሦስት ዓመት ሀገራዊ የፍትሕ ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ ውስጥ በህብረተሰቡ ውስጥ ላሉ ባህላዊ የፍትህ ሥርዐቶችን ትኩረት ሰጥቷል። እነዚህን ማጠናከርና ህብረተሰቡ በተገቢው መንገድ እንዲገለገልባቸው ማድረግ ቀዳሚ ትኩረቱ መሆኑን የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር ኤርሚያስ የማነብርሃን ይናገራሉ፡፡ በዚህም “አፊኒ”ን ጨምሮ በየአካባቢው ያሉ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዐቶች በህብረተሰቡ ዘንድ ያላቸው ተቀባይነት የጎላ በመሆኑ በልፅገውና ዳብረው አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ብሎም የፍትሕ ሥርአቱ ያሉበትን ክፍቶች መሙላት እንዲችሉ ሚኒስቴሩ ሙያዊና ሌሎች ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል። ይህ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዐት ከዘመናዊው የፍትሕ ሥርዐት የሚለይበት የራሱ ባህሪያት ያሉት ሲሆን ሲዳማዎች ታላቅ ከበሬታን የሚሰጡትና የፍቅር ሸማቸውን የሚቋጩበት ድንቅ መገለጫቸው ነው፡፡ ዘመነኛው የፍርድ ችሎት ምስክሮችን ቆጥሮ ማስረጃዎችን አጣርቶ ፍርድ ይሰጣል፣ በዚህ የፍርድ ሂደት ውስጥ በምስክርና በማስረጃ የረታ ይፈረድለታል የተረታ ደግሞ ይፈረድበታል። በክርክር መሀል አሸናፊና ተሸናፊን የሚለየው ሕጋዊ እውነት ነው፤ የሚቀርበው መረጃና ማስረጃ ነው። በርግጥ በመደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚሰየሙ ችሎቶች ምስክሮችን እንደየሃይማኖታዊ አስተምህሮታቸው መሀላ እንዲፈፅሙ ማድረጋቸውን ልብ ይሏል ፡፡   የሲዳማ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክትልና የባህል ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳዊት ዳንጊሶ እንደሚያስረዱት በ“አፊኒ ሶንጎ” ላይ በዳኝነት የሚሰየሙት ሽማግሌዎች ወይም በሲዳማዎች አጠራር “ጪሜሳ”ዎች ናቸው። የዳኝነት ስርአቱን ሲያከናውኑ መነሻቸውም መደምደሚያቸውም “ሀላሌ” ብቻ ነው፡፡ እነኚህ የዕድሜ ፀጋን ከብልሀት ጋር ደርበው የለበሱ ሽማግሌዎች በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ተአማኒነትና ክብር ያላቸው ሲሆኑ እውነትን መርምሮ የማውጣት ጥበብን የተካኑ ናቸው፡፡ “ሀላሌ”ን ለማግኘት አብዝተው ይተጋሉ፣ ለፍርድም የማይቸኩሉ በሳሎች በመሆናቸው ጉዳዩ ውስብስብ ቢሆን እንኳ እውነቱን ሳያገኙ ለፈርድ አይቸኩሉም። እውነት የዳኝነት ሥርዐቱ የህልውና መሠረት ነውና ሳይታክቱ ይመረምራሉ፤ ይተጋሉ፡፡ በዚህ መሠረት ስለሚሰሩ በሁሉም ወገን ቅቡልነት ያለው ፍትሕን ያሰፍናሉ፡፡ የዳኝነት ሥርዐቱ መደምደሚያ ዕርቀ ሠላም ነውና ሁለቱም ወገኖች ይታረቃሉ፤ ሽማግሌዎችም ዳግም ቅራኔ ውስጥ እንዳይገቡ መርቀዋቸው፤ “ሀላሌ”ም ከሰዎች ልቦና እንዳይርቅ “ማጋኖ”ን ተማፅነው ጉዳዩን ይቋጩታል፡፡ ኢትዮጵያ ሠላሟ እንዲጸና አብሮነትና ወንድማማችነት ደምቆ እንድትቀጥል የሲዳማ አፊኒን ጨምሮ በየአካባቢው ያሉ ሌሎች ሀገር በቀል የእርቅና የሰላም እሴቶች በእጅጉ እንደሚያስፈልጓት አሌ የማይባል ሀቅ ነው። ሆኖም እንደ ሀገር ቀደም ባሉት ጊዜያት ለባህላዊ እሴቶችና ለሀገር በቀል እውቀቶች ትኩረት ተነፍጎ በመቆየቱ የመደብዘዝ እጣ ፈንታ ገጥሟቸው ነበር፡፡ “አፊኒ”ም ለሰላምና ለአብሮነት ባለው ፋይዳ ልክ ሳይጎለብት፣ በሚገባ ሳይተዋወቅና ህዝቡም በሚፈለግው ልክ ሳይጠቀምበት ቆይቷል፡፡ አሁን ግን መንግስት ለባህል እሴቶች በሰጠው ትኩረት ለ“አፊኒ” ዘመን የሰመረለት ይመስላል፡፡ በክልሉ ባሉ 656ት ቀበሌያት “አፊኒ ሶንጎ”ዎች ይሰየማሉ፡፡ “ሀላሌ”ም በነዚህ ሸንጎዎች ላይ ይነግሳል፡፡ ያኔ በሲዳማ ሰማይ ሥር ወትሮም የማትጠፋው የእውነት ፀሐይ ደመናዋን ገልጣ ይበልጥ ትደምቃለች፡፡ ነባር “አፊኒ ሶንጎ”ዎች ባሉባቸው ቀበሌያት ሸንጎዎቹ በላቀ ደረጃ ህዝቡ እንዲገለገልባቸው ዕውቅና የሚሰጣቸው ሲሆን በሌሉባቸው ቀበሌያት ደግሞ በአዲስ መልክ ይቋቋማሉ፡፡ እነዚህ ሸንጎዎች ከጋብቻ ፍቺ በስተቀር ሁሉንም ፍትሐብሔራዊ ጉዳዮችን እንዲሁም በግል አቤቱታ የሚቀርቡ የወንጀል ጉዳዮችን እንደሚመለከቱ የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መብራቴ መስፍን ይገልጻሉ ፡፡ በወረዳና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮችም የወረዳ “አፊኒ ሶንጎ” የሚቋቋም ሲሆን ይህም ከቀበሌ “አፊኒ ሶንጎ” በይግባኝ የሚመጡ ጉዳዮችን ተመልክቶ ውሳኔ ይሰጣል ፡፡ በክልል ደረጃ ደግሞ “ሞቴቴ ሶንጎ” ወይም በባህላዊ አመራርነት ውስጥ ከፍተኛውን እርከን የሚይዙት “ሞቴ”ዎች የሚመሩት ሸንጎ ይደራጃል፡፡ ይህ ሸንጎ እንደ ቁንጮነቱ የሚመለከታቸው ጉዳዮችም ከፍ ያሉ ናቸው ፡፡ ለአብነት የወሰን ግጭቶችን እንዲሁም የአለባበስ፣ የለቅሶ፣ የሠርግና የጥሎሽ ሥርዐቶአች ላይ ውሳኔ የማስተላለፍ ሥልጣን የሚኖረው ሲሆን እንደ ክልል የባህላዊ ዳኝነት ሥርዐቱን አካሄድ የሚከታተልና የማረቅ ኃላፊነት በእጁ የተጣለበት እንደሆነም ነው አቶ መብራቴ የሚያስረዱት፡፡ በዚህ ውስጥ የመደበኛ ፍርድ ቤቶች ሚና የሸንጎዎችን የመጨረሻ ውሳኔ ተፈፃሚነት መከታተልና ማስገደድ ይሆናል ፡፡ “አፊኒ”ን በዚህ ልክ ማላቅ ባህላዊ እሴትን አስጠብቆ ከማስቀጠል የተሻገረ ትሩፋት አለው፡፡ ፍትሕን ፍለጋ ከማሳው ተነጥሎ ወደ ወረዳ ማዕከላትና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ለሚሄድ አርሶ አደር ትልቅ እፎይታም ነው፡፡ በአጭር ጊዜ ከቀዬው ባለ ሸንጎ ተዳኝቶ ሠላም አውርዶ ወደቤቱ ይመለሳል፤ ልማቱንም ይቀጥላል፡፡ ይህም አርሶ አደሩ ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት በመመላለስ ያጠፋ የነበረውን ጊዜ፣ ገንዘብና ጉልበቱን በማዳን ትኩረቱን ማሳው ላይ ብቻ እንዲያደርግ ያስችለዋል፡፡ ለመደበኛ ፍርድ ቤቶችም ቢሆን ያለባቸውን የሥራ ጫና በማቅለል ቀልጣፋና የላቀ አገልግሎት እንዲሰጡ ምቹ መደላድልን ነው የሚፈጥረው ፡፡ የሲዳማ ህዝብ ጠብቆ ካቆያቸውና ተጠቃሽ ከሆኑ የ“አፊኒ ሶንጎ” ዎች መካከል ልዩ ከበሬታ የሚሰጠውና ልዕልና ያለው ሸንጎ አለ። ይህም “አቦ ዎንሾ ” ይባላል፡፡ “አቦ ዎንሾ” በክልሉ ዎንሾ ወረዳ የሚገኝ ስፍራ ሲሆን 16 ተከታታይ ትውልዶችም የተቀባበሉት የዳኝነት ሥርዐት ይካሄድበታል፡፡ ሥፍራው በሰው ልብ ውስጥ ያለ የሀሰትና የክፋት ተራራ እንደ በረዶ የሚያቀልጥ መንፈሳዊ ኃይል እንዳለው ይነገራል ፡፡ በቀጣይ “አቦ ዎንሾ”ን በስፋት እንመለስበታለን!  
ተምሳሌቷ አርሶ አደር - ወይዘሮ ሃረጉ ጎበዛይ
Mar 16, 2025 192
በተካ ጉግሳ መቀሌ (ኢዜአ) አርሶ አደር ሃረጉ ጎበዛይ በትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን የራማ ዓዲ አርባዕተ ወረዳ ነዋሪ ናቸው። በአካባቢያቸው የግብርና ስራን የጀመሩት ከአካባቢ ጥበቃ ነው። ወትሮም ወደ ግብርና ስራ ያስገባቸው የሚኖሩበት አካባቢ ገላጣና አቧራማ ከመሆን ባለፈ ለኑሮ የማይመችና አረንጓዴ ልማትን በእጅጉ የሚሻ አካባቢ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ነበር። አርሶ አደሯ ከግብርና ስራ ውጪ ሌላ ስራ ያለም አይመስላቸው። ግብርናን ያልማሉ፤ ግብርናን ይኖራሉ፤ በግብርና ህይወታቸውን ለመቀየር ያቅዳሉ። ሆኖም ወደውት ሊገቡበት ያሰቡት የግብርና ስራ ከአካባቢው ሁኔታ ጋር ተዳምሮ ግዙፍ ካፒታል እንደሚጠይቃቸው አስበዋል። አስበውም አልተቀመጡም በአንድ ወቅት አንዳች ነገር ለማድረግ ወሰኑ። በቅድሚያ አርሶ አደሯ ሃረጉ አዕምሮ ላይ የተከሰተው ነገር እጄ ላይ ምን አለ የሚለው ነበር። በወቅቱ እጃቸው ላይ የነበረው ከሁለት ጥማድ መሬታቸው ያገኙት አንድ ኩንታል ዳጉሳ ነበር። ያንን አንድ ኩንታል ዳጉሳ ገበያ ወስደው በ1 ሺህ 500 ብር ይሸጡታል። ከዚያም ባገኙት ገንዘብ ምን ቢሰሩ እንደሚያዋጣቸው ለመወሰን በግላቸው የአዋጪነት ጥናት አደረጉ። ከዚያም ካላቸው ሁለት ጥማድ መሬት ግማሽ ሄክታር የሚሆነውን መስኖን በመጠቀም የማንጎ ተክልን ቢያለሙ ምን ያህል ሊጠቀሙ እንደሚችሉ ቀድመው አሰቡ። አርሶ አደሯ ወደ ማንጎ ልማቱ ከመግባታቸው በፊት ሊተገብሩት የሚገባ አንድ ብርቱ ጉዳይ እንዳለ አመኑ። እሱም አካባቢያቸውን በማልማት ወደ አረንጓዴነት መቀየር ቀዳሚው ነበር። ከአካባቢያቸው አስተዳደር ጋር በመነጋገርም ያንን ድንጋያማ፣ የተቦረቦረና የግብርና ስራ ናፍቆት ጦም ያደረ መሬት ወደ አረንጓዴነት የመቀየር ተግባራቸውን ተያያዙት። በዚህም የተቦረቦሩ የመሬት ክፍሎችን በአፈር የመሙላትና የመደልደል ስራም የእርሳቸው ነበር። እዚህ ጋር ከባዱ ስራ የነበረው አፈር ከሌላ ቦታ ማመላለሱ አድካሚ ሆኗል፤ ነገር ግን አርሶ አደሯ ግን ያስቀመጡት ራዕይ ከፊት ለፊታቸው እየታያቸው ነበርና የድካም ስሜቱ ሳያግዳቸው ተግባሩን በብቃት ፈፀሙት። ባለቤታቸውን ከጎናቸው በማድረግም ቀድሞ በግማሽ ሄክታር ላይ ለማልማት አስበውት የነበረውን ልማት በጦም አደር መሬት ጋር ወደ 12 ሄክታር በማሳደግ ከማንጎ በተጨማሪ የአፕል ችግኞችን በመትከል ወደ ሰፊ ልማት ተሸጋገሩ። አርዓያነታቸው ተነሳሽነትን የፈጠረላቸው የአካባቢው አርሶ አደሮችም ከእርሳቸው ጋር ወደ ልማቱ በድፍረት እንዲገቡ አደረጓቸው። አንድም ቀን ለሚያለሙት ልማት ዘመናዊ ማዳበሪያ ተጠቅመው እንደማያውቁ የሚናገሩት ወይዘሮ ሃረጓ የተፈጥሮ ማዳበሪያን የሁልጊዜ የግብረና ስራቸው አጋዥ ግብዓት በማድረግ እየተጠቀሙ እንደሚገኙ ይናገራሉ። ይህንንም በወንዝ ውሃ ከሚወሰድ ደለል በማጠንፈፍ በማዘጋጀት እንደሚጠቀሙና ምርትና ምርታማነታቸውን እንዳሳደገላቸው ይገልጻሉ። አርሶ አደሯ የግብርና ባለሙያዎች የሚሰጧቸውን ሙያዊ ምክር በመቀበል እየተገበሩት የሚገኘው የግብርና ስራ በየጊዜው ውጤታማ እያደረጋቸው እንደሚገኝ አዘውትረው ይገልፃሉ። በቅርቡም ከአርባ ምንጭ በማምጣት የተከሉት ሙዝ ከአካባቢው አፈር ጋር መስማማቱን በግብርና ባለሙያዎች መረጋገጡን ገልፀዋል። ስለሆነም ዘሩን በማባዛት ጥቅም ላይ ለማዋል ዕቅድ እንዳላቸው አመልክተዋል። አርሶ አደሯን ተምሳሌት ካደረጓቸው ተግባራት አንዱ ያለሙትን የማንጎም ሆነ የአፕል ችግኝ ለአካባቢው አርሶ አደሮች በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ለተግባር አጋሮቻቸው ህይወት መለወጥ የበኩላቸውን እየተወጡ መገኘታቸው ነው። ለዚህም ይመስላል የሴት አርሶ አደር ወይዘሮ ሃረጉን ተሞክሮ ለማየት የግብርና ባለሙያዎች የምርምር አባላት የተካተቱበት ቡድን ሰሞኑን በአርሶ አደሯ ማሳ የተገኙት። በዚህም በራማ ዓዲ አርባዕተ ወረዳ የአርሶ አደሯን የተቀናጀ ልማት ምልከታ ተከናውኗል።   በወቅቱም የክልሉ እርሻ ምርምር ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ገብረአምላክ በዛብህ(ዶ/ር) የአርሶ አደሯ ሥራ ግርምትን እንደፈጠረባቸው መስክረዋል። በወርሃ ግንቦትና ሰኔ አፕልና ማንጎ በየቀኑ ሁለት የጭነት ተሽከሪካሪዎችን ወደ ተለያዩ የክልሉ ከተሞች እና ወደ አዲስ አበባ ገበያዎች በመላክ በአማካይ በየቀኑ ከአንድ መኪና እስከ 650 ሺህ ብር ትርፍ የሚያገኙ መሆናቸውን ሲገልፁ ደግሞ የወይዘሮዋን ጥረትና ተምሳሌትነት በደንብ ያሳያል ብለዋል። አርሶ አደሯ የገበያ ትስስራቸውን እስከ አዲስ አበባ በመዘርጋታቸው የገበያ ችግር እንደሌለባቸው ዘወትር ሲናገሩ እንደሚደመጡም መስክረዋል። የአካባቢው አርሶ አደሮች እየተደራጁ እንዲያለሙና በገበያ ትስስሩ በመጠቀም የገበያ ችግራቸውን እንዲቀርፉ እያደረጉ መሆኑንም አመልክተዋል። የአካባቢው አርሶ አደሮችም ዘወትር ይህንኑ ምስክርነት ይሰጧቸዋል።   ከነዚህም አንዱ አርሶ አደር ተክላይ ገብረ ይጠቀሳሉ። አርሶ አደሯ እያከናወኑት ያለው ጠንካራ ስራ ለእሳቸውም ተነሳሽነት ፈጥሮላቸው በመስኖ ልማት በመሳተፍ የእርሻ ማሳቸውን እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል። አርሶ አደሯ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ተነሳሽነትን ከማውረስ በተጨማሪ የአካባቢውን ፀጋ በማልማት ተጠቃሚ መሆን እንድንችል ፈር ቀዳጅ እንደሆኑላቸውም አርሶ አደር ተክላይ መስክረዋል። በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ የመስኖና ሆልቲካልቸር ዳይሬክተር አቶ ሀይለ ታደለ በበኩላቸው፡ የአርሶ አደሯ እንቅስቃሴ መንግስት ቀጣይነት ያለው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማትን ለማስፋት እያደረገ ያለውን ጥረት ለመደገፍ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው ብለዋል። አካባቢውን የፍራፍሬ ልማት ማእከል/ስፔሻላይዝ/ የማድረግ ዓላማ እንዳላቸው የሚናገሩት ወይዘሮ ሃረጉ ጎበዛይ፣ አሁን ላይ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ 50 ሺህ የማንጎ እና የአፕል ችግኞችን እያፈሉ ለአካባቢው አርሶ አደሮች በተመጣጠኝ ዋጋ ለማከፋፈል እንደተዘጋጁም ገልፀዋል።
ፋጭኤ - ቂምና ቁርሾ በመሻር ሰላምና አብሮነትን የሚያጸና!
Mar 10, 2025 241
በያንተስራ ወጋየሁ (ከኢዜአ ዲላ ቅርንጫፍ) በቀደመው ትውልድ በማህበረሰቡ አልያም በግለሰብ የተፈጸመ በደል በይቅርታ ሳይሻር ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ይመጣል። መሸጋገሩ ሳይበቃ ቂምና ቁርሾ ወልዶ ከተግባሩም ከታሪኩም በእጅጉ የራቀው የኋልኛው ትውልድ ጭምር ዋጋ ሲከፍልበት ማየት የተለመደ ነው። በተለይ በነጠላ ትርክት በትውልድ ስነ ልቦና አሁን የተፈፀመ ያህል እንዲሰማ ተደርጎ መተረኩ በማህበረሰብ ትስስር ከዚያም ባለፈ በጋራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ላይም ከፍተኛ ጫና ሲያሳድር ቆይቷል። በዚህም አያሌ ሊቅና ደቂቅ ትልቁን ሀገራዊ ስዕል መመልከት ትተው በመንደርና በጎጥ ፖለቲካ ሲጠመዱና ሲሸጎጡ ይስተዋላል። ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት የተፈጠሩ አለመግባባቶችንና በደሎችን በምክክር በመፍታት ጠንካራ ሀገራዊ አንድነትን ለመገንባት እየተሰራ ነው። ህብረ ብሔራዊነት የሰፈነበት ሀገረ መንግስት ግንባታን ለማጠናከርም ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ልዩነትን በምክክር ለመፍታትና የህዝቦችን አብሮነት ለማጠናከር እየተሰራ ነው። ይህን ስራ ለማጠናከር የሚረዱ ባህላዊ ስርአቶችም በህብረተሰቡ ውስጥ አሉ። "ፋጭኤ" ለእዚህ አንድ ማሳያ ነው። በጌዴኦ ብሔር ተወላጆች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ቂምና ቁርሾ ማሻሪያ ባህላዊ ሥርአት ነው። የብሔሩ ተወላጆች ስርዓቱ ከማህበረሰብ እስክ ግለሰብ የደረሱ አለመግባባቶች፣ ቅሬታዎችና ያደሩ ቂምና ቁርሾዎችን በአግባቡ ለይቶ በመፍታት ዘላቂ ሰላምን ለማውረድ ይጠቀሙበታል። በሀገራችን በተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ የዳኝነትና የግጭት አፈታት ሥርዓቶች አሉ። በጌዴኦ ብሔር ያለው የግጭት መፍቻ ሥርአት "ጋፌ" ተብሎ ይጠራል። ይሁንና የፋጭኤ ስርዓት ከባህላዊ የዳኝነትና የግጭት አፈታት በእጅጉ የሚለይና የሚልቅ እንደሆነ ይነገራል። በፋጭኤ ሥርአት በዳይ ተበዳይ ላይኖር ይችላል። በደሉ በየትኛውም ዘመን የተፈጠረ ቢሆንም በፋጭኤ ስርዓት ዋናው ነገር ሰላም ማውረድና ማህበራዊ ፍትህን ማረጋገጥ ነው። በተለይ በደሉ ቂምና ቁርሾ ፈጥሮ ትውልድ እንዳይግባባ ካደረጋ የባህል ሽማግሌዎች በሶንጎ ተቀምጠው በደሉን በጥንቃቄ በመለየትና በማውገዝ ችግሩ በይቅርታ እንዲፈታ ያደርጋሉ። ይህንን ሃሳብ የጌዴኦ ባህላዊ የባሌ አስተዳደር መሪ አባ ገዳ ቢፎሚ ዋቆ በተጨባጭ ምሳሌ ያስጠናክራሉ። ከመቶ ዓመታት በፊት "አኮ ማኖዬ" የተሰኝ በሴቶች የበላይነት የሚመራ ሥርዎ መንግስት ጌዴኦን ያስተዳድር ነበር። ስርዓቱ ወንዶችን ይጨቁናል በሚልና በወንዶች በተቀነባበረ የውሸት ሴራ ንግስቲቱን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደልሥርዎ መንግስቱን እንዲገረሰስ ተደርጓል። በወንዶች የተፈጸመው ይህ ጭካኔ የተሞላበት ግድያ ለብዙ መቶ ዓመታት በብሔሩ የስርዓተ ጾታ መስተጋብር ውስጥ የተዛባ ትርክት በመፍጠር በሴቶች ዘንድ ቂምና ቁርሾ እንዲቋጠር አድርጎ እንደነበር ነው አባ ገዳ ቢፎሚ የገለጹት። እሳቸውን ጨምሮ የባህላዊ ስርዓቱ መሪዎች የባህላዊ ስርዓት መከወኛ ስፍራ በሆነው "ሶንጎ" ላይ ቁጭ ብለው በደሉን ገምግመውና መርምረው ችግሩን እንደለዩ አንስተዋል። በወቅቱ የተፈጸመውን በደል ለህዝብ በማቅረብና የበደሉ ገፈት ቀማሽ የሆኑ ሴቶችን በአደባባይ ይቅርታ በመጠየቅ ቂምና ቁርሾ እንዲሽር ማድረጋቸውን ይናገራሉ። ይህም በዞኑ ሁለንተናዊ እድገትን ለማረጋገጥ የተባበረ አቅምን ለመጠቀም አስችሏል። "ፋጭኤ ከቂምና ቁርሾ እንዲሁም ከበደል የመንጻት ባህላዊ ስርአት ነው" የሚሉት ደግሞ የሀገር በቀል እውቀቶች ተማራማሪው አቶ ፀጋዬ ታደሰ ናቸው። እንደእሳቸው ገለጻ ስርአቱ በጌዴኦ ብሔር ተወላጆች ዘንድ በስፋት አዲስ ዓመት ከመሻገሩ በፊት የሚፈጸም የአንድነት ማጎልበቻ ስርዓት ነው። ፋጭኤ ከሰው ባለፈ ከፈጣሪም ጋር ሰላም የሚወርድበት ስርዓት መሆኑን ነው የሚናገሩት። በተለይ ድርቅና ረሃብ ሲከሰት፣ ዝናብ በዝቶ ወንዝ ሙላት ህዝብን ሲያስችግር እንዲሁም ወረርሽኝ፣ ሰው ሰራሽ አደጋዎችና ጦርነት የህብረተሰቡን አኗኗር አደጋ ውስጥ ከጣሉ ፈጣሪ ተቆጥቷል በሚል የፋጭኤ ስርዐት ይከናወናል። በዚህ ወቅት የባህላዊ ስርዓት መሪዎች (የሶንጐ አስተዳዳሪዎች) አካባባዊ ሁኔታን ገምግመው ህዝቡ ባህላዊ ክዋኔዎች በሚካሄድበት ስፍራ ወጥቶ በሰው፣ በእንስሳትና በተፈጥሮ ላይ ያደረሰውን በደል በመናዘዝ ይቅርታ እንዲጠይቅና ከፈጣሪው ጋር እንዲታረቅ የፋጭኤን ሥርዐት ያካሂዳሉ። ይህም በህብረተሰቡ ውስጥ ሰላምና እርቅ እንዲወርድ ከማድረጉ ባለፈ ዛሬ ዞኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ ጭምር የሚታወቅበት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እንዲጠናከር መሰረት መጣሉን እጩ ዶክተር ፀጋዬ ይገልጻሉ። በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የባህል እሴቶችና የሀገር በቀል እውቀቶች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ እስከዳር ግሩም በበኩላቸው እንዳሉት በኢትዮጵያ ፋጭኤን ጨምሮ ከ100 በላይ ሀገር በቀል እውቀቶች እንዳሉ ተለይተዋል። ይህም ኢትዮጵያን በባህል እሴቶች ተጠቃሽ እንደሚያደርጋት ነው የገለጹት። ማህበረሰቡ በመኖር ሂደት ውስጥ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ቁርኝት፣ የሚጠቀምባቸው የግጭት አፈታት ሥርዓቶች፣ የዘመን አቆጣጠር፣ የባህል ህክምናና የእድ ጥበብ ውጤት እንዲሁም የእርከንና የግብርና ልማት ሥራዎች ለሀገር በቀል እውቀቶች ተጠቃሽ ማሳያ መሆናቸውን ነው የገለጹት። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ መንግስት ለሀገር በቀል እውቀትና እሳቤዎች ተገቢ ትኩረት መስጠቱ ባህላዊ እሴቶች እንዲበለጽጉ እድል ፈጥሯል። ለብሔራዊ የምክክር መድረኩም ተጨማሪ አቅም ያጎናጸፈና ልምድ እየሰጠ መምጣቱን ነው ያነሱት። እነዚህ ባህላዊ እውቀቶች በስፋት ጥቅም ላይ እንዲውሉና የአንዱ ባህል ለሌላው ተሞክሮ እንዲሆን ማስተዋወቅና ማስፋት ያስፈልጋል። ለእዚህ ደግሞ የመገናኛ ብዙሀን ተቋማት ሚና የጎላ መሆኑን ነው የገለጹት። በማህበረሰቡ ዘንድ በስፋት ጥቅም ላይ የሚውሉ በተለይም ለሀገራዊ አንድነትና ሰላም ፋይዳ ያላቸው ባህላዊ እሴቶች ከተደበቁበት ወጥተው እንዲተዋወቁ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ነው ወይዘሮ እስከዳር የተናገሩት። በተለይ እንደ ፋጭኤ ያሉ ቂምና ቁርሾን በማስቀረት ለሰላምና ለህዝብች አብሮነት ዋጋቸው ከፍ ያሉ ባህላዊ ሥርአቶችን ማጎልበት፣ ማስተዋወቅና በስፋት ጥቅም ላይ ማዋል የሁሉም ሃላፊነት መሆኑን ነው የገለጹት።
በ30 ደቂቃዎች ሽልብታ ያለፉ 48 ሰዓታት
Mar 1, 2025 652
የብዙሃኑ ቀለሜ ተማሪዎች ሕልም ነው- ሃኪም መሆን። በአካባቢ ማህበረሰቡ ዘንድም ቢሆን ብዙን ጊዜ ጎበዝ ተማሪ ዕድል ፈንታው 'ዱክትርና' ተደርጎ ይሳላል። እናም ኤልሳቤጥ ግና ከለጋነቷ ጀምሮ የቀለሜነት ጉዞዋ የተመለከቱ በዙሪያዋ የተኮለኮሉ ወዳጅ ዘመዶች 'ሃኪምነት' ተመኙላት። ከቅድመ መካነ-አዕምሮ የትምህርት ሕይወቷ 'ዶክተር ትሆኛለች' አሏት። እርሷም ተመኘች፤ ራዕይ ሰነቀች። ለምኞቷ ስኬትም ጊዜና ሁኔታን አዋደደች። ቀለሜነቷን በማንበብ ዋጀች። በትናንት ትኩረት የዛሬዋን ጡብ ደረደረች፤ የነገ መሻቷን ሰራች። በአላውቅም ስሜት ለማወቅ ጣረች፤ ለሌሎች አርዓያ ሆና ቀጠለች-ኤልሳቤጥ አርዓያ። እነሆነ ዛሬ ሕልሟን ጨበጠች፤ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ትምህርት ቤት 3 ነጥብ 93 ውጤት ይዛ ተመረቀች። ዝም ብሎ መመረቅ ብቻ ግን አይደለም፤ ቀለሜዋ ኤልሳቤጥ የዩኒቨርሲቲውን የዓመቱን የወርቅ ሜዳሊያ ወሰደች። የትናንት የሃኪም ባለራዕይዋ፤ የዛሬዋ የጠቅላላ ሃኪምነት ምሩቋ ዶክተር ኤልሳቤጥ አርዓያ 'ሕክምና ባልገባ ኖሮ ምን እሆን ነበር' ብላ ትጠይቃለች። በምትወደው ሙያ ተምሮ ለመመረቅ፤ ላለፈችበት ውጣ ውረድ ቤተሰብ የነበራቸው ውለታ በኤልሳቤጥ አንደበት ቃላት ያንሳሉ። በሕክምና ትምህርት ቤት (ለዚያውም ከፍተኛ ውጤት አምጥቶ ለመመረቅ) የቀለሜ ነት ዳራ መያዝ ብቻውን በቂ አይደለም። ቀልብ፣ ጊዜና ትኩረትን በቅጡ መጣጣም እንዳለበት ትናገራለች። እንደ አለመታደል ሆኖ በኤልሳቤጥና የዘመነ-ትምህርት ጓዶቿ ጊዜ የኮቪድ-19 ወረርሽን ተከስቷል። ይህም ከሰባት ዓመታት ወራት ጉዳይ የሆነው የትምህርት ዘመናቸው ወደ ስምንት ዓመታት እንዲገፋ ምክንያት ሆነ። ሆኖም የስምንት ዓመታት የዩኒቨርሲቲ ቆይታ በሥነ ምግባርና በዕውቀት ጎልብተው ከመመረቅ አላገደንም ትላለች። በተግባር ተኮር ትምህርት ቆይታዋ በተለይም ሕፃናት ታካሚ ስትመለከት ከፉኛ እንደፈተናት የምትገልፀው ኤልሳቤጥ፤ ይህ ግን ብርቱና ጠንካራ ማንነት ለመገንባት አስችሏታል። ሕክምና ትምህርት ምን ያህል ዕለታዊ የጥናት ዝግጅት የሚጠይቅ ከባድ ትምህርት ዘርፍ እንደሆነ ኤልሳቤጥና ጓደኞቿ ምስክር ናችው። በተለይም የመጨረሻዎቹ ዓመታት በጊዜ ዕጦት ፈተና የታጀቡ ናቸው ትላለች። "48 ሰዓታትን በ30 ደቂቃዎች ሽልብታ ብቻ ያሳለፍንበት ጊዜ ነበር" ትላለች ኤልሳቤጥ። ያም ሆኖ በአስተማሪዎችም ድጋፍ፣ በተማሪዎችም ብርታት አስቸጋሪ ቀናት አልፈው፤ ኤልሳቤጥ በማዕርግ ተመረቃለች። ከትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር በርሐኑ ነጋ እና ከጤና ሚኒስትሯ ዶከትር መቅደስ ዳባ ዕጅ ክብርና ሽልማቷን አጥልቃለች። የብዙ ዓመታት ዕንቅልፍ ዕጦት፣ የሰርክ ጥረትና ግረት ትሩፋቷን ዛሬ ተቋድሳለች። የትምህርትንም፤ የሕይወትንም ፈተና ተቋቁማ ድል የተቀዳጀችው ዶክተር ኤልሳቤጥ 'ሁሉንም አውቃለሁ ማለት የውድቀት መነሻ ነው' ትላለች። አዳዲስ ነገሮችን ለማወቅና ለተሻለ ነገር ሁሌም መትጋት ይገባል ትላለች። "ሴቶች ይችላሉ፤ ለስኬት የሚያግዳቸው ነገር የለም" የምትለው ኤልሳቤጥ፤ ምንም ጫና ቢኖር ሕልምን ለመኖር 'እችል ይሆን' ብሎ ማቅማማት እንደማያሻ ትመክራለች። እንደ ኤልሳቤጥ ሁሉ ዕልፍ ብርቱ ቀለሜዎች ፈተናዎችን ሳይበግራቸው ወሳኙን የትምህርት ምዕራፍ ተሻግረዋል። አካል ጉዳቱ ሳይበግረው ከነኤልሳቤጥ አርዓያ ጋር ከፍተኛ ውጤት ይዞ የተመረቀው ዶክተር ቢኒያም ኢሳያስ ለዚህ አብነት ነው።   ያለፉት ዓመታት ያለድካምና ስልቸታ ሰርክ የማጥናትና የመማር ዕለታዊ ተግባራቱ የዛሬዋን ውብ ቀን እንዳመጣችለበት ቢኒያም ይናገራል። ከራሱ ጥረት ባሻገር በጓደኞቹ የተደረገለትን ድጋፍም አልዘነጋም። ዘመኑ ዕድልም፤ ፈተናም እንዳመጣ የሚገልፀው ዶክተር ቢኒያም፤ ዕውቀትንና ክህሎትን በቀላሉ ማበልፀግ የሚያስችሉ ምቹ የቴክኖሎጂ አፈራሽ ዕድሎች እንዳሉ ይናገራል። አዎ በርካቶቹ እንደ ምሩቃን ሃኪሞቹ ኤልሳቤጥና ቢኒያም ፈተናን በድል ቀይረው በአድዋ ድል መታሰቢያ ዋዜማ ተመርቀዋል፤ ድላቸውን አጣጥመዋል። አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ትምህርት ቤት 53 በሕክምና ዶክትሬት፣ 21 በጥርስ ህክምና፣ 23 ደግሞ አንስቴዥያ በድምሩ 197 ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቋል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 946
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 1075
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 1396
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 2672
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 326
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 1065
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 2419
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 44745
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 39616
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 26639
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 23968
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 22280
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 20614
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 20259
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 19893
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 44745
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 39616
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 26639
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 23968
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የካቲት እና ኢትዮጵያ
Feb 26, 2025 418
በአየለ ያረጋል   በየክፍላተ-ዓለሙ ዓመታት በወራት ሲመነዘሩ የራሳቸው መልክና መገለጫ ይኖራቸዋል። እንደየንፍቀ ክበቡ ወቅቶች የራሳቸው ጸባይ፣ ክዋኔ፣ ትውስታና ትዕምርት ይቸራቸዋል። ኢትዮጵያ ብቸኛዋ ባለ13 ወር ጸጋ ናት። ከጎርጎሮሳዊያኑ የዘመን ቀመርም ሰባት ዓመት ከስምንት ወራት ልዩነት አላት። በባሕር ሃሳብ ምሁራን የኢትዮጵያን ወቅቶች መጸው(መኸር)፣ ሐጋይ(በጋ)፣ ፀደይ(በልግ) እና ክረምት በሚል አራት ወቅቶችና አውራኅ ይከፍሉታል። ሁሉም አውራኅ፣ እያንዳንዱ ወራት በራሳቸው ተፈጥሯዊና ባህላዊ ቀለማትን ይጎናጸፋሉ። የወራቱ ቅላሜና ሕብርነት ልዩ መልክዓ-ኢትዮጵያን ይፈጥራል። ከዘመን መባቻው መስከረም እስከ ማዕዶተ-ዘመኗ ጳጉሜን ወራቱ በሰማይና በምድሩ ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ውቅራቸው ግላዊ ገጽታ ይነበብባቸዋል። የኢትዮጵያ ወራት ስያሜ ከመልክና ግብራቸው ይመነጫል። ከሁሉም ወራት ግን ከታሪካዊ ሁነቶች አንጻር የካቲት ልዩ ገጽታ አለው። አሁን ወቅቱ በጋ ወይም ሐጋይ ነው። ወርኅ የካቲትንም የሐጋይ አውራኅ ደማቁ ገጽ ነው። በኢትዮጵያ ታሪክና ፖለቲካ ውስጥ ወርኅ የካቲትን ያክል በየታሪክ ህዳጉ የኢትዮጵያን ዕጣ ፈንታ የወሰነ ወቅት ያለ አይመስልም። የካቲት የበጋ ወርኅ አልፎ የበልግ ጊዜ መግቢያ ነውና የቋንቋ ሊቃውንቱ 'የካቲት'ን ስያሜ 'የመከር ጫፍ መካተቻ፤ የበልግ መባቻ " ይሉታል። የመኸር ምርት የሚከተትበት ነው። በኢትዮጵያ ዘመን ስሌትም መንፈቅ ዓመት ወይም ስድስተኛው ወር ነው። ወርኅ የካቲት በመካከለኛው ዘመን ዝነኛውን ንጉስ አፄ ሠርፀድንግልን፣ የአድያምሰገድ ኢያሱን ልጅ ዳግማዊ አፄ ዳዊት(አድባር ሰገድን)፣ “የዘመናዊት ኢትዮጵያ ጠንሳሽ ናቸው” የሚባሉትን አፄ ቴዎድሮስንና ንግስት ዘውዲቱን አንግሷል። በሌላ በኩል ኢማም አሕመድ ኢብራሂምን(ግራኝ አህመድ)፣ አፄ ሚናስን፣ እቴጌ ጣይቱን፣ እቴጌ መነንን፣ ንጉስ ወልደጊዮርጊስን፣ ራስ ደስታ ዳምጠውን፣ ራስ አሉላ እንግዳን እና ሌሎች የዓድዋ ብሔራዊ የጦር ጀግኖችን አሳርፏል። ከኪነ-ጥበብ መስክ ደግሞ ወርኅ የካቲትን ያህል የሞት ዶፍ የወረደበት ወቅት እንደሌለ ብዙዎቹ ይስማማሉ። ለአብነትም ሞገደኛው ብዕረኛ አቤ ጉበኛ እረፍት የካቲት 2፣ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር የካቲት 12፣ ጸጋዬ ገብረመድህን የካቲት 18፣ ማሞ ውድነህ የካቲት 23፣ እንዲሁም ተወዳጁ ደራሲና ጋዜጠኛ በዓሉ ግርማ እንደወጣ የቀረው የካቲት 24 ነበር። የካቲት በርካታ የምንኮራባቸው ሰዎች የተወለዱበትና በሞት ያጣንበትም ወር ነው። የካቲት ታላቅ የሰማዕትነት ወር ነው፤ በ1929 ዓ.ም 30 ሺህ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በጅምላ በአካፋና በዶማ በግፍ የተጨፈጨፉት በወርኅ የካቲት ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የጣሊያን ወራሪን በማሳፈር ለጥቁር ሕዝቦች ቀንዲል የሆነውን የዓድዋ ድል የተቀዳጀችው በየካቲት መገባደጃ ወቅት ነበር። መልከ-ብዙው ዓድዋ ድል፤ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ተከውኗል። በዚያች ተዓምረኛ ዕለት በዓድዋ ተራሮች መንደር መድፎች አጓርተዋል፤ መትረየሶች አሽካክተዋል፤ እሳት ወርዷል፤ ጥይት ዘንቧል፤ ጎራዴ ተመዟል፤ ጦር ተሰብቋል። በጥቅሉ የክቡር ሰብዓ ዘሮች ደም ተገብሯል። የዓድዋ ድል ህያውነት፣ እንቆቅልሽነት፣ አድማስ ዘለል ታሪክነት፣ የዓለም ነፀብራቅነት፣ አፍሪቃዊነት፣ ኢትዮጵያዊነት ተዘርዝሮ አያልቅም፤ በዓድዋ ጦርነት የተመዘገቡ የይቅርታ፣ የፍቅርና የርህራሄ እሴቶች ከጥቁር ሕዝቦች ድልነት አሻግረው ለእያንዳንዱ ሰው ድል አድርገውታል። ከየካቲት ድሎች ዓድዋ ይድመቅ እንጂ ቅድመ-ዓድዋም ሆነ ድኅረ-ዓድዋ ጦርነት ደማቅ ድሎች ተመዝግበዋል። ለምሳሌ ኢትዮጵያ በወርኅ የካቲት የግብጽን ወረራ በጉራ፣ የሶማሊያ ጦርነትን በካራማራ፣ ድል ተቀዳጅታለች። የካቲት 12 ጭፍጨፋ እና የካቲት 23 የዓድዋ ድልን ጨምሮ በኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ የማንነት፣ የሀዘን ሁነቶችና ተፃራሪ ታሪኮችን አስተናግዷል ይኸው ወርሃ የካቲት። የ1928ቱ የጣሊያን ወረራ በሽሬ፣ በተንቤን እና በአምባራዶም የጦር ሜዳዎች የተከለከለ መርዝ በኢትዮጵያዊያን ላይ ተርከፍክፎ እንዲቃጠሉ መደረጉም የታሪክ ድርሳናት እማኝ ናቸው። ወርኅ የካቲት በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ታላላቅ አብዮቶች፣ ታላላቅ ድሎች ተከውነውበታል። ለኢትዮጵያ ሕልውና እንደ ክብር የደም ግብር የቀረበበት፣ በየጋራና ሸንተረሩ የትውልድ መስዕዋትነት የተከፈለበት ጊዜ ነው። የካቲት የድልና የዕድል፤ የደምና ገድል ወር ነው። አሳዛኝም፤ አስደሳችም! የካቲትና የኢትዮጵያ ታሪክ ግንኙነት ድል የተገኘበት፣ መጥፎ ጠባሳዎችንም ያተምንበት ወቅት በመሆኑ ወርኅ የካቲትን በግጥምጥሞሽ የተሞላ፤ ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ጋር ተነጥሎ የሚታይ አይደለም። የካቲት ወር 2010 ዓ.ም በኢህአዴግ ላይ የነበሩ አመጾች የተባባሱበትና ፖለቲከኞች ከእሥር የተፈቱበት ነው። የካቲት 8 ቀን 2010 ዓ.ም ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከኃላፊነት ለመልቀቅ ለፓርቲው መልቀቂያ ደብዳቤ ያቀረቡበት ነው። ከኢትዮጵያ አልፈው እንደ ዓድዋ ያሉ ለጥቁር ሕዝቦች ትግል አብነት የሆኑ ታሪኮች የተፈጸሙበት፣ አብዮት የተካሄደበትና የኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ የተወሰነባቸው ክስተቶችን ያስተናገደ ወር እንደሆነ ያነሳሉ። በኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ የማንነት፣ የሀዘን ሁነቶችን ማስተናገዱን አስተናግዷል። የወርሃ የካቲት ሁነቶች ተጻራሪ ታሪኮች እንደሆኑ የካቲት 12 እና የካቲት 23ን ለአብነት ይጠቀሳሉ። በርግጥ ወርኅ የካቲት ከኢትዮጵያ አልፎ በአጠቃላይ የመብትና ነፃነት ትግሎች የተስተናገዱበት ሲሆን በአገረ- አሜሪካ ጥቁሮች ለእኩልነትና ነፃነት የታገሉበት ወቅት በመሆኑ የታሪካቸው አካል በማድረግ ያከብሩታል። ለመሆኑ ወርኅ የካቲት ከኢትዮጵያ ታሪክና ፖለቲካ ጋር የመጣባቱ ምስጢር ምን ይሆን? ለጉዳዩ አመክንዮ የሰጡ የታሪክ ምሁራን ወርሃ የካቲት ገበሬው የሚያርፍበት፣ ወንዞች ደርቀው ሰው የሚገናኝበት በመሆኑ እንዲሁም የጾም ወቅት መሆኑ የውጭ ጠላቶች አስልተው እንደሚመጡ ጠቅሰው፤ ለአብነትም በሰንበትና በፆም ወቅት የተደረገውን የአድዋ ጦርነት ያነሳሉ። ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው ህዝብ ገበሬ የሆነባት ኢትዮጵያ ካሏት 13 ወራት መካከል ወርኃ የካቲት ለገበሬው ጥጋብ፣ ለመንግስታት ደግሞ የግብር መሰብሰቢያ ወር መሆኑን በማውሳት። ወርኃ የካቲት ምርት ተሰብስቦ ጎተራ የሚገባበት፣ ሰርግ የሚሰረግበት፣ ሽፍታ የሚበረታበት ወቅት ነው። በ'ግብር ገብር! አልገብርም!' በሚል ግብግብ የገበሬ አመጽ የታየበት ወር መሆኑ ይወሳል። በሌላ በኩል ወቅቱ ተማሪዎች ከአንደኛው መንፈቅ ዓመት ወደ ሁለተኛው የሚሸጋገሩበት ነው። በዚህም ተማሪዎችም ለንቅናቄ ይነሳሳሉ። በ1960ዎቹ የተደረገውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመሬት ለአራሹ፣ የዴሞክራሲ፣ የኃይማኖትና የብሔር ጥያቄዎችን ያነሱበትና አብዮት የቀሰቀሱበት እንደነበር የታሪክ ምሁራን ይናገራሉ። የካቲት በርካታ የምንኮራባቸው ሰዎች የተወለዱበትና ያጣንበትም ወር መሆኑን ለምን ብለን ባንጠይቅም፤ ግጥምጥሙ ግን አጃይብ ያሰኛል። ኢትዮጵያ በየካቲት ወር ባሳለፈቻቸው ታሪኮች ልትማር፣ ትውልዱም ታሪኩን ሊያውቅ ይገባል።
የበይነ-አፍሪካዊያን ትስስር ተምሳሌት - አሊኮ ዳንጎቴ 
Feb 20, 2025 389
ቀደምት ፓን አፍሪካዊነት አቀንቃኞች አንዱ ህልማቸው በኢኮኖሚና ፖለቲካ የተሳሰረች፣ ራስ በቅ አፍሪካን ዕውን ማድረግ ነበር። ጥሬ ዕቃዎቿ ላይ እሴት የሚጨምሩ ኢንዱስትሪዎች ባለቤት የሆነች፣ ከውጭ ምርቶች ጥገኝነት የተላቀቀችና በምግብ ራሰ በቅ የሆነች፣ በበይነ-ቀጣናዊ የኢኮኖሚና ንግድ የተሳሰረች አፍሪካን ዕውን ማድረግ ነበር ጽኑ መሻታቸው። ለዚህም አንዳንድ የአፍሪካ መንግስታት ከቅኝ ግዛት ነጻ በወጡ ማግስት ጀምሮ በፖለቲካዊና በኢኮኖሚ ራስን ለመቻል ስትራቴጂ ነድፈዋል። ለዚህ ደግሞ ግዙፍ አፍሪካ በቀል ኩባንያዎችን መስርቶ ምርታማነትን መጨመር፣ ሀገራትን በልማት ማስተሳሰር እና ብርቱ አህጉር አቀፍ የግል ዘርፍ መገንባት የሞከሩ አሉ። ባለሙያዎችም ከመንግስት መር ኢኮኖሚ ልማት ይልቅ ለዘላቂ ዕድገት የግል ዘርፍ መራሽ አፍሪካ አቀፍ ኢኮኖሚ መገንባት እንደሚያሻ ይወተውታሉ። የአፍሪካ የኢኮኖሚ ውህደትና ትስስር በአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ ወቅት ቢቀነቀንም አህጉራዊ የስምምነት ማዕቀፍ ሆኖ የወጣው በአፍሪካ ሕብረት አስቸኳይ ውሳኔ በፈረንጆቹ 2018 ነበር። ይሄውም አፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ነው። ከ2021 ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ጀምሯል። ስምምነቱን 54 አባል ሀገራት ፈርመዋል። 48ቱ ሀገራት በሕግ መወሰኛ ምክር ቤቶቻቸው አፅድቀውታል። የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ማዕቀፍ ታዲያ የግል ዘርፋን የሚያበረታታ ነው። ይህ ደግሞ በአፍሪ ሀገራት የሚገኙ ከበርቴዎች ከትውልድ ሀገራቸው ተሻግረው በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱና አፍሪካ አቀፍ ኢኮኖሚያዊ ትስስርና ተጠቃሚነት እንዲጎለብት መልካም ዕድል ይዞ ይመጣል።   ናይጄሪያዊው ከበርቴ አሊኮ ዳንጎቴ የአፍሪካ የግሉ ዘርፍ ቁንጮ ናቸው። በፎርብስ መጽሔት መረጃ በተያዘው ዓመት የ67 ዓመቱ ቢሊየነር ዳንጎቴ 23 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ሀብት አካብተዋል። ዳንጎቴ በአፍሪካ ኢንቨስመንትቻውን እያሰፉ ነው። ይህ እንቅስቃሴያቸው ደግሞ የራስ በቅና የበይነ-አፍሪካዊያን ትስስር ተምሳሌቱ ቱጃር ያሰኛቸዋል። አሊኮ ዳንጎቴ ከሰሞኑ ወደ አዲስ አበባ ጎራ ብለው ለኢትዮጵያ አዳዲስ መረጃዎችን አብስረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ጋር መክረዋል። ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) ጋር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በኢትዮጵያ ያላቸውን የሲሚንቶ ምርት መጠን በዕጥፍ ለማሳደግ ወስነዋል። ከማዕድን(ሲሚንቶ) በተጨማሪም በሌሎችች ኢንቨስትመንት አማራጮች ለመሰማራት የአዋጭነት ገበያውን እየፈተሹ ስለመሆኑ እንዲሁ። ለአብነትም የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ መገንባትን ጨምሮ የግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን በሚያሳድጉ ዘርፎች ለመሰማራት አቅደዋል። በስኳር ልማት እንዲሁ። ናይጄሪያዊው የአፍሪካው ቀዳሚው ባለሃብት አሊኮ ዳንጎቴ በሲሚንቶ፣ የነዳጅ ማፈላለግ፤ የማዕድን ማውጣት፤ የማዳበሪያ እና የተፈጥሮ ጋዝ ማጓጓዝ ስራዎች ላይ በስፋት ተሰማርተዋል። ናይጄሪያን ጨምሮ በ20 የአፍሪካ ሀገራት በቢሊዮኖች ዶላር የሚገመት ኢንቨስትመንት አፍስሰዋል። ለአብነትም በሲሚንቶ ዘርፍ ከናይጄሪያ በተጨማሪ በኢትዮጵያ፣ ታንዛንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ዛምቢያ፣ ሴኔጋል፣ ካሜሮን፣ ኮንጎ ሪፐብሊክ፣ ጋና እና ኮትዲቭዋር የሲሚንቶ ፋብሪካ ገንብተዋል። በናይጄሪያ ሌጎስ የአፍሪካ ግዙፉን የዳጅ ማጣሪያ ገንብተዋል። ስገንብተዋል። የነዳጅ ማጣሪያው ጋና እና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ በአፍሪካ ሀገራት ነዳጅ ይልካል። ኩባንያው የአውሮፕላን ነዳጅን ወደ አውሮፓ ለመላክም አቅዷል። ከባድ ናፍጣ የመላክ እቅድ አለው። የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣረያ የአፍሪካ የነዳጅ ጥገኝነት ለመቀነስ ተስፋ ተሰንቆበታል። ኩባንያቸው በግብርና፣ ምግብ ማቀነባበሪያ፣ በስኳር፣ በፋይናንስ አገልግሎት፣ መሰረተ ልማትና ኢነርጂ፣ ማዳበሪያ፣ በምግብ እና መጠጥ እና ቴሌኮሙኒኬሽን፣ ኮንስትራክሽን እና ሌሎች ዘርፎች በኢንቨስትመንት ተሰማርቷል። አሁንም አፍሪካን እያካለለ ነው። ቱጃሩ ዳንጎቴ በብረታ ብረት፣ በታዳሽ ኃይል፣ በጤና እና ፋርማሲዩቲካል ዘርፎችም ያላቸውን ኢንቨስትመንት በአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የማስፋት ግብ ይዘዋል። የአሊኮ ዳንጎቴ እንቅስቃሴ ከቀደምት ፓን አፍሪካዊያን ህልም ጋር የተጣጣመ ነው። አፍሪካን በአፍሪካ በቀል ኢንዱስትሪ ማልማት፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ከውጭ ምርት ጥገኝነትን መቀነስ፣እሴት የተጨመረባቸወን የአፍሪካ ምርቶች ወደ ሌሎች አህጉራት መላክና አፈሪካዊያን ማስተሳሰር ለዚህ ሁነኛ አብነት ናቸው። ዳንጎቴን መሰል የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ለአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ ውጤታማነት ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ። ለአህጉራዊ አጀንዳዎች ስኬት የግሉ ዘርፍ ምሰሶ በመሆኑ ለአፍሪካ ዘላቂ ዕድገት የመንግስታት እና የግሉ ዘርፍ እጅና ጓንት መሆንን ይጠይቃል። የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች የሁልጊዜም ምክረ ሀሳብ ነው።  
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም