አርእስተ ዜና
በምስራቅ ሸዋ ዞን ከ80 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በቦሎቄ ልማት ተሸፍኗል
Sep 2, 2025 7
አዳማ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፦በምስራቅ ሸዋ ዞን በኩታ ገጠም የሚለማ ከ80 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በኤክስፖርት ቦሎቄ መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። ዞኑ ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቦሎቄ ምርት ለማግኘት በትኩረት እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል። የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገዬ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ አብዛኞቹ የዞኑ ወረዳዎች ለቆላ ጥራጥሬ ሰብሎች አመቺ መሆናቸውን ገልጸዋል። በዞኑ የግብርና የኤክስፖርት ምርቶች ላይ በትኩረት እየሰራን ነው ያሉት አቶ አብነት በተለይ የቦሎቄና የማሾ ሰብሎች በሰፊው እንደሚመረቱ ተናግረዋል። በዚህም የዞኑ አርሶ አደሮች በማህበር ተደራጅተው በቦሎቄ ልማት ላይ በብዛት እንዲሳተፉ የማድረግ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። በዚህም በዞኑ ከ80 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም በኤክስፖርት ቦሎቄ ልማት መሸፈኑን ተናግረዋል። አዳሚ ቱሉ፣ ጂዱ ኮሞቦልቻ፣ ቦሰት፣ ሎሜ፣ ፈንታሌ፣ ዱግዳና ቦራ ወረዳዎች የቦሎቄ ልማት በኩታገጠም በስፋት የለማባቸው ወረዳዎች መሆናቸው ተናግረዋል።
2017 ዓ.ም ውስብስብ ፈተናዎችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪ ድሎች የተመዘገቡበት ነበር-ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር)
Sep 2, 2025 27
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017 (ኢዜአ)፡- 2017 የበጀት ዓመት ውስብስብ ፈተናዎችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪና እመርታዊ ድሎች የተመዘገቡበት እንደነበር የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሰጡት መግለጫ፤ የተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ለኢትዮጵያ በእጅጉ ስኬታማ ዓመት መሆኑን አስታውቀዋል። ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) አክለውም፥ 2017 የበጀት ዓመት ውስብስብ ፈተናዎችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪና እመርታዊ ድሎች የተመዘገቡበት ነበር ብለዋል። ድሎቹ ብዙ ሊነገርላቸው የሚገባ፣ትምህርትም የሚቀሰምባቸው እንዲሁም ለቀጣይ ሀገራዊ ድሎች እንደወረት የሚወሰዱ መሆናቸውን ጠቁመዋል። መጪው አዲስ ዓመትም እነዚህን ድሎች በይበልጥ የምናሰፋበት ብሎም ተግዳሮቶቻችንን የምንቀንስበት እንዲሆን ሰፊ ዕቅድ ተቀምጧል ሲሉ አመላክተዋል። ይህን መሠረት በማድረግም ወደ ንቅናቄ መገባቱን ነው የተናገሩት። የጳጉሜን ወር ወደ አዲሱ ዓመት የምንሸጋገርበት ድልድይ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ቀናቱ በተለይም ለኢትዮጵያውያን በእጅጉ ልዩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣዮቹ የጳጉሜን ቀናት በሀገር አቀፍ ደረጃ በተናበበ አካሄድ እንደሚከበሩም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን የተሰጠውን አገር የማስተዋወቅ ተልዕኮ በስኬት አጠናቆ ተመልሷል-ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን
Sep 2, 2025 21
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን የተሰጠውን አገር የማስተዋወቅ ተልዕኮ በስኬት አጠናቆ ተመልሷል ሲሉ የመከላከያ ሠራዊት ስነልቦና ግንባታ ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን ገለጹ። በሩሲያ ሞስኮ በተዘጋጀው የማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብቷል።   ማርቺንግ ባንዱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፈያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። የመከላከያ ሠራዊት ስነልቦና ግንባታ ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን በወቅቱ፣ የማርችንግ ባንድ ቡድኑ አባላት ተልዕኳቸውን በአግባቡ ያሳኩ የሀገር ጀግኖች መሆናቸውን ተናግረዋል። በዓለም አቀፍ መድረክ ኢትዮጵያን በአግባቡ በማስተዋወቅ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እና ሀገርን ያኮራ ተግባር ማከናወናቸውን በመጥቀስ፥ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል። የሀገር ኩራት መሆኑን ከዚህ ቀደም በብዙ ሥራዎቹ ያስመሰከረው የመከላከያ ማርችንግ ባንድ፥ በፌስቲቫሉ ላይ ያሳየው ሙያዊ ዲሲፒሊን ለዓለም አብነት የሚሆን ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ሩሲያ ባዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የመከላከያ ማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ መሳተፏ ወታደራዊ የልምድ ልውውጥ ለማድረግና ትብብርን ለማጠናከር ጉልህ አበርክቶ መጫወቱን ተናግረዋል።   የመከላከያ ኪነ-ጥበባት ሥራዎች ዳይሬክተር ኮሎኔል ማንያህለዋል ታደለ ዝግጅቱ የተሳካ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከአፍሪካ፣ ከአውሮፓ እና ከኤስያ የተወጣጡ የበርካታ ሀገራት የማርችንግ ባንድ አባላት መሳተፋቸውን ተናግረዋል። ዘመናዊ የሙዚቃ መሳሪያን ተጠቅመን ባህላዊ ዘፈኖቻችንን እና ባህላዊ ጭፈራዎቻችንን አዋህደን በማቅረብ ዓለምን ያስደነቀ ሥራ ሠርተናል ብለዋል።   የማርችንግ ባንዱ ሉዑክ አባል የሆነችው ሻምበል ሔለን አለሙ፤ መድረኩ ልምዳችን ያካፈልንበት እና ከእነሱም ልምድ የወሰድንበት ነበር ብላለች፡፡ ሌላኛዋ የባንዱ ሉዑክ አባል ሐምሳ አለቃ ሒወት አሰፋ፤ ፌሰቲባሉ የአገራችን ባህልና ወግ ለአለም ከማስተዋወቅ ባሻገር ሩሲያውያን በአገራቸው ጉዳይ በአንድ ልብ መካሪ በአንድ ቃል ተናጋሪ መሆናቸውን አይተናል ብላለች።      
ዩኒቨርሲቲው በአራት የትምህርት መርሃ ግብሮች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘ
Sep 2, 2025 27
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአራት የትምህርት መርሃ ግብሮች ዓለም አቀፍ እውቅና ማግኘቱን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ደረጀ እንግዳ (ዶ/ር) ገለጹ። ዶክተር ደረጀ እንግዳ እውቅናውን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና የሚሰጣቸው የትምህርት መርሃ ግብሮች ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲው አሜሪካ ከሚገኘው ዓለም አቀፍ የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ እውቅና ሰጭ ቦርድ /ABET/ በአራት የትምህርት መርሃ ግብሮች እውቅና ማግኘቱን አስታውቀዋል። እውቅናውን ያገኘው በመጀመሪያ ዲግሪ በሚሰጣቸው የባዮ-ቴክኖሎጂ፣ የምግብ ሳይንስ እና ሥነ ምግብ፣ የኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ እና የጂኦሎጂ የትምህርት መርሃ ግብሮች መሆኑን ጠቅሰዋል። እውቅናው ለተመራቂ ተማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ የሥራ ዕድሎችን እንደሚከፍት እና የትምህርት መረጃቸው ዓለም አቀፍ እውቅና እንዲኖረው የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ከመላው ዓለም ተማሪዎችን ተቀብሎ እንዲያስተምር ያስችለዋል ብለዋል።  
የጳጉሜን ቀናት በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማክበር ዝግጅት ተደርጓል-የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Sep 2, 2025 43
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፦የ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት ዋዜማ አምስቱ የጳጉሜን ቀናት በሀገር ዓቀፍ ደረጃ በተለያየ ዝግጅትና ስያሜ ለማክበር የዝግጅት ስራ መጠናቀቁን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል። ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት፥ የ2018 ዓ.ም የአዲስ ዓመት ዋዜማ አምስቱ የጳጉሜን ወር ቀናት አከባበር ዝግጅትና ስያሜን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ በ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት መሸጋገሪያ አምስት የጳጉሜን ቀናትም በተለያዩ ዝግጅቶች ለማክበር ዝግጅት መደረጉን አመልክተዋል። በዚህም ጳጉሜን 1 የጽናት ቀን፣ጳጉሜን 2 የህብር ቀን፣ ጳጉሜን 3 የእምርታ ቀን፣ ጳጉሜን 4 የማንሰራራት ቀን እና ጳጉሜን 5 የነገው ቀን በሚል እንደሚከበሩ ገልጸዋል። ቀናቱም በሀገር ዓቀፍ ደረጃ በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች እንደሚከበሩ ጠቁመዋል።
የሚታይ
2017 ዓ.ም ውስብስብ ፈተናዎችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪ ድሎች የተመዘገቡበት ነበር-ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር)
Sep 2, 2025 27
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017 (ኢዜአ)፡- 2017 የበጀት ዓመት ውስብስብ ፈተናዎችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪና እመርታዊ ድሎች የተመዘገቡበት እንደነበር የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሰጡት መግለጫ፤ የተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ለኢትዮጵያ በእጅጉ ስኬታማ ዓመት መሆኑን አስታውቀዋል። ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) አክለውም፥ 2017 የበጀት ዓመት ውስብስብ ፈተናዎችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪና እመርታዊ ድሎች የተመዘገቡበት ነበር ብለዋል። ድሎቹ ብዙ ሊነገርላቸው የሚገባ፣ትምህርትም የሚቀሰምባቸው እንዲሁም ለቀጣይ ሀገራዊ ድሎች እንደወረት የሚወሰዱ መሆናቸውን ጠቁመዋል። መጪው አዲስ ዓመትም እነዚህን ድሎች በይበልጥ የምናሰፋበት ብሎም ተግዳሮቶቻችንን የምንቀንስበት እንዲሆን ሰፊ ዕቅድ ተቀምጧል ሲሉ አመላክተዋል። ይህን መሠረት በማድረግም ወደ ንቅናቄ መገባቱን ነው የተናገሩት። የጳጉሜን ወር ወደ አዲሱ ዓመት የምንሸጋገርበት ድልድይ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ቀናቱ በተለይም ለኢትዮጵያውያን በእጅጉ ልዩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣዮቹ የጳጉሜን ቀናት በሀገር አቀፍ ደረጃ በተናበበ አካሄድ እንደሚከበሩም ጠቁመዋል።
የጳጉሜን ቀናት በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማክበር ዝግጅት ተደርጓል-የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Sep 2, 2025 43
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፦የ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት ዋዜማ አምስቱ የጳጉሜን ቀናት በሀገር ዓቀፍ ደረጃ በተለያየ ዝግጅትና ስያሜ ለማክበር የዝግጅት ስራ መጠናቀቁን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል። ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት፥ የ2018 ዓ.ም የአዲስ ዓመት ዋዜማ አምስቱ የጳጉሜን ወር ቀናት አከባበር ዝግጅትና ስያሜን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ በ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት መሸጋገሪያ አምስት የጳጉሜን ቀናትም በተለያዩ ዝግጅቶች ለማክበር ዝግጅት መደረጉን አመልክተዋል። በዚህም ጳጉሜን 1 የጽናት ቀን፣ጳጉሜን 2 የህብር ቀን፣ ጳጉሜን 3 የእምርታ ቀን፣ ጳጉሜን 4 የማንሰራራት ቀን እና ጳጉሜን 5 የነገው ቀን በሚል እንደሚከበሩ ገልጸዋል። ቀናቱም በሀገር ዓቀፍ ደረጃ በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች እንደሚከበሩ ጠቁመዋል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ሀሳቡን የሚያጋራበት የአጭር መልዕክት ማስተላለፊያ ኮድ ይፋ ሆነ
Sep 2, 2025 55
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017 (ኢዜአ)፦ከዛሬ ጀምሮ ለ33 ቀናት የሚቆይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን በተመለከተ ያለውን ሃሳብና መልዕክት የሚያጋራበት 8120 አጭር መልዕክት ማስተላለፊያ ኮድ ይፋ ሆኗል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር ዜጎች መልካም ምኞታቸውን የሚገልጹበት "የትውልድ አሻራ ዲጂታል የብስራት መልዕክትና ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት" በሚል ስያሜ መልዕክት እንዲያስተላልፉ የሚያስችል ነው።   በዚህ ወቅት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) እንዳሉት፥ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የወል ትርክታችንና ላባችንን ቀለም ክንዳችንን ደግሞ እንደብዕር አድርገን የፃፍነው መፅሀፍ ነው። ሕዳሴ ግድብ ከተባበርን የዕድገት ማማ ላይ መውጣት እንደምንችል ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። ህብረተሰቡ ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ የበኩሉን ሲወጣ መቆየቱን ጠቁመው፤ ኢትዮ ቴሌኮም በ"8100 A" ላይ በመላክ በተከታታይ ለሶስት ዙር የድጋፍ ማሰባሰብ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። ከዛሬ ጀምሮ ህብረተሰቡ ደስታውንና ስሜቱን የሚያጋራበት 8120 በእጅ ስልክ በመላክ መልዕክት ማጋራት ይችላል ነው ያሉት። የአጭር መልዕክት ማስተላለፊያ ኮዱ ከዛሬ ነሃሴ 27 ቀን 2017 እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 ድረስ ባሉት ጊዜያት ህብረተሰቡ ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን መሆን ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ በተመለከተ በአጭር መልዕክት ሃሳቡን በመግለፅ አሻራውን ለታሪክ መዘክርነት ማስቀመጥ የሚችልበት ነው። በአጭር መልዕክት ማስተላለፊያ ኮዱ 1 ቁጥር መላክ አምስት ብር ድጋፍ ማድረግና በህብረት ችለናል የሚል መልዕክት ያለው ሲሆን፤ 2 ቁጥር ደግሞ የ10 ብር ድጋፍና ታላቁ ሕዳሴ ግድብ የብልፅግና አሻራ የሚል መልዕክት ያለው መሆኑ ተገልጿል። 3 ቁጥር የ15 ብር ድጋፍና ግድባችን የአሸናፊነት ድል አክሊል እንዲሁም 4 ቁጥር የ100 ብር ድጋፍና ግድባችን የአባይ ዘመን ትውልድ የተጋድሎ ሰንደቅ የሚል መልዕክት ያላቸው መሆኑ ተጠቁሟል። በተጨማሪም ህብረተሰቡ የራሱን መልዕክት ሲልክ 20 ብር ድጋፍ እንደሚያደርግም ነው የተገለፀው። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ያለውን ስሜት፣ሃሳብና መልዕክት ለታሪክ ከትቦ ማስቀመጥ የህዝባዊ ተሳትፎ አካል በመሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ መልዕክቱን በመግለፅ ለትውልድ የሚያስተላልፍበት ፕሮጀክት ማስፈለጉ ተገልጿል።
የመከላከያ ማርችንግ ባንድ በሩሲያ ቆይታው የሀገርን ባህል እና ሙያዊ ብቃቱን ለዓለም በማስተዋወቅ አኩሪ ተግባር ፈጽሟል-ሜጀር ጀነራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን
Sep 2, 2025 78
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017 (ኢዜአ)፦የመከላከያ ማርችንግ ባንድ ሩሲያ ባዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ የሀገርን ባህልና ገፅታ እና ሙያዊ ብቃቱን ለዓለም በማስተዋወቅ አኩሪ ተግባር መፈጸሙን የመከላከያ ሠራዊት ስነልቦና ግንባታ ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን ገለጹ። በሩሲያ ሞስኮ በተዘጋጀው የማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብቷል።   ማርቺንግ ባንዱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። የመከላከያ ሠራዊት የስነልቦና ግንባታ ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን በዚሁ ወቅት፣የማርችንግ ባንድ ቡድኑ አባላት ተልዕኳቸውን በአግባቡ ያሳኩ የሀገር ጀግኖች መሆናቸውን ተናግረዋል። በዓለም አቀፍ መድረክ ኢትዮጵያን በአግባቡ በማስተዋወቅ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እና ሀገርን ያኮራ ተግባር ማከናወናቸውን በመጥቀስ፥ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል። የሀገር ኩራት መሆኑን ከዚህ ቀደም በብዙ ሥራዎቹ ያስመሰከረው የመከላከያ ማርችንግ ባንድ፥ በፌስቲቫሉ ላይ ያሳየው ሙያዊ ዲሲፕሊን ለዓለም አብነት የሚሆን ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ሩሲያ ለ5 ቀናት ባዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የመከላከያ ማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ መሳተፏ ወታደራዊ የልምድ ልውውጥ ለማድረግና ትብብርን ለማጠናከር ጉልህ አበርክቶ መጫወቱን ተናግረዋል። የመከላከያ ኪነ- ጥበባት ሥራዎች ዳይሬክተር ኮሎኔል ማንያህለዋል ታደለ ዝግጅቱ የተሳካ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከአፍሪካ፣ከአውሮፓ እና ከእስያ የተወጣጡ የበርካታ ሀገራት የማርችንግ ባንዶች የተሳተፉበት መሆኑን ተናግረዋል። ዘመናዊ የሙዚቃ መሳሪያን ተጠቅመን ባህላዊ ዘፈኖቻችንን እና ባህላዊ ጭፈራዎቻችንን አዋህደን በማቅረብ ዓለምን ያስደነቀ ሥራ ሠርተናል ብለዋል። የማርችንግ ባንዱ ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ዘመቻ በዲ በበኩላቸው፥ ቡድኑ በሠራቸው የሙዚቃ ሥራዎች እና የመድረክ ላይ እንቅስቃሴዎቹ ከፍተኛ አድናቆት ማግኘቱን ገልፀዋል። ቡድኑ የሀገራችንን ብሔሮች ብሔረሰቦች አለባበስ፣ ዜማ፣ ውዝዋዜና ሌሎች የጥበብ ባህሎች በማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።  

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎችን የሰላም እሴቶች ግንባታ ይበልጥ ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቷል
Sep 2, 2025 72
ድሬደዋ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፡-የምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎችን የሰላም እሴቶችን ግንባታ ይበልጥ ለማጠናከር ትኩረት መሰጠቱ ተገልጿል። የምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎችን የሰላም እሴቶችን ግንባታና ግንኙነትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል የምክክር መድረክ በድሬደዋ እየተካሄደ ነው። የምክክር መድረኩን የፌደሬሽን ምክር ቤት ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ነው። የፌደሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዘሐራ ሁመድ እና የሰላም ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። በተጨማሪም የምስራቅ ተጎራባች ክልሎች የሆኑት የሶማሌ፣ የአፋር፣ የሐረሪ፣ የምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ኦሮሚያ ዞኖችና የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች እንዲሁም የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች እየተሳተፉ ነው። በቀጠናው ያለውን ዘላቂ ሰላም ለማፅናት እና የተጎራባች ክልሎቹን የመንግስታት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ መድረክ መሆኑን የፌደሬሽን ምክር ቤት የህዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ሞገስ ጀምበሬ ለኢዜአ ገልጸዋል። እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ፥ ተጎራባች ክልሎቹ የፈጠሩትን የጋራ ፎረም በማጎልበት በአካባቢው ተቀናጅተው የጀመሩትን የብልፅግና ጉዞ ለማጠናከር ያግዛቸዋል።
የህዳሴ ግድብ የአባይን የዘመናት ህልም ወደ ፍሬ ማፍራት እንዲሸጋገር አድርጓል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 1, 2025 234
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአባይን የዘመናት ህልም እና እንጉርጉሮ ወደ ሚጨበጥ ውጤት እንዲቀየር ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የ“ኩስመና ታሪክ ማብቂያ” በሚል ርዕስ የጉባ ላይ ወግ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያውያን ለበርካታ መቶ ዓመታት በአባይ ወንዝ ተጠቅሞ ለማደግ ፍላጎቶች እንደነበሯቸው እና ሙከራዎችን እንዳደረጉ አመልክተዋል። ሙከራዎቹ በገንዘብ እጥረት፣በቴክኒክ አቅም ውስንነት፣ የጂኦ ፖለቲካ አለመመቸት እና ብዙ ምክንያቶች ሙከራዎቹን እንዳይሳኩ ማድረጉን ተናግረዋል። አባይን አስመልክቶ ያሉ በርካታ ስነ ጽሁፎች፣ ግጥሞች፣ ዘፈኖች እና እንጉርጉሮዎች በሀብቱ መጠቀምን ሳይሆን ባለመጠቀም ውስጥ ያለን ቁጭት አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። በወንዙ ሀብት ተጠቅሞ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግንባታ ማከናወን የተቻለው ከጂኦ ፖለቲካዊ ኩስመና ወደ ተሻለ ቁመና ሽግግር ውጤት መሆኑን ነው የገለጹት። መንግስት ጂኦ ፖለቲካዊ ኩስመና በፍጹም አንቀበልም እኛን አይመጥነንም፣ ኢትዮጵያ ካላት ስፋት አንጻር ለህዝቡ ታሪክ የሚበጅ አይደለም በማለት ትርክቱን ለመቀየር ወደ ስራ መግባቱን አመልክተዋል። በጂኦ ፖለቲክሱ የተሻለ ቁመናን ለመያዝ እየተከናወነ ባለው ስራ እና ሌሎች አስቻይ ሁኔታዎች ምክንያት የዘመናት ህልም፣የዘመናት እንጉርጉሮና የዘመናት ለቅሶ ወደ ፍሬና ወደ ውጤት እንዲቀየር ማስቻሉን ተናግረዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #Ethiopia #ኢትዮጵያ #ህዳሴ #የአባይግድብ
ሕዳሴን እንደ መደበኛ ፕሮጀክት ሳይሆን እንደ የዘመናት ቀንበር መስበሪያ፤እንደ የታሪክ መታጠፊያ መስመር አድርጌ ነው የማየው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 1, 2025 157
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዳሴ ግድብን እንደ መደበኛ ፕሮጀክት ሳይሆን የዘመናት ቀንበር መስበሪያ፤የታሪክ መታጠፊያ መስመር አድርጌ ነው የማየው አሉ። "የኩስመና ታሪክ ማብቂያ" በሚል ርዕስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ጋር ባደረጉት የጉባ ላይ ወግ፤ከሕዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ክትትልና ስኬታማ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ ገለጻ አድርገዋል። በገለጻቸውም፤አንድን ሥራ ጀምሮ ለመጨረስ፤በቅድሚያ ጨርሶ የማየት ዐቅም ያስፈልጋል ብለዋል። ያንን ቀድመን ጨርሰን ያየነውን ነገር በርካቶች እንዲያዩት ደግሞ በከፍተኛ ዲሲፕሊን መትጋት ይፈልጋል ነው ያሉት። በዚሁ መሠረት ላለፉት ሰባት ዓመታት ወደ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በመመላለስ በንቃት ክትትል ማድረጋቸውን አንስተዋል። የክትትል ሥራ ለማንኛውም የሥራ መሥክ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤የተጉ እናቶች ልጆጃቸውን ለፍሬ እንዳበቁ ሁሉ፤ የተጉ ሠራተኞች ደግሞ ሀገራቸውን ለፍሬ አብቅተዋል፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እየሆነ ያለውም ይህ ነው ብለዋል። የሕዳሴ ግድብን እንደ መደበኛ ፕሮጀክት ሳይሆን የዘመናት ቀንበር መስበሪያ፤ የታሪክ መታጠፊያ መስመር አድርጌ ነው የማየው ሲሉም ገልጸዋል። እንደሚታወቀው ዓባይ ለዘመናት ሲሄድብን ኖሯል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የሕዳሴ እሳቤ ውኃ እንዲሄድብን ሳይሆን ጀልባ ሠርተን እኛ በውኃ ላይ እንድንሄድበት ነው፤በዚህም ዓሣ ማጥመድ እንድንችል ነው፤ ያስቀረነውን አፈር መርምረን ወርቅ ይኑረው ወይም አይኑረው መለየት እንድንችል ነው ሲሉ አብራርተዋል። ዓባይን ጨርሶ ኢትዮጵያ ውስጥ የታሪክ እጥፋት ማረጋገጥ የመጨረሻ ጸሎቴና ምኞቴ ነበር ሲሉም ገልጸዋል። ሲጀመር ፈጣሪ ትልቁን ዓባይ ለኢትዮጵያ አምኖ የሰጠው በፍትሐዊነት እንደምትጠቀመው ስላመነባት ነው ብዬ አምናለሁ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። በዚህ አግባብ ነው ግድባችንን ለፍሬ ያበቃነው፤በሱዳንም ሆነ በግብጽ ያሉ ግድቦች አንድም ሊትር አልቀነሱም በቂ መረጃ አለን፤ ወደ ፊትም እንዳይቀንሱ ነው የእኛ ፍላጎት በዚሁ አግባብ እንሠራለን ብለዋል። ከተደመርን እና ከተጋን ያሰብነው ይሳካል፥ ለዚህም የሕዳሴው ግድብ ማሳያ ነው በማለት ጠቅሰዋል። #Ethiopian_News_Agency #Ethiopia #ኢትዮጵያ #ኢዜአ
የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በፅናት በማለፍና ወደ ዕድል በመቀየር የብልጽግና እሳቤዎች ወደ ውጤት እየተቀየሩ ነው- አቶ አደም ፋራህ
Sep 1, 2025 135
ሀዋሳ ፤ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ) ፡-የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በፅናት በማለፍና ወደ ዕድል በመቀየር የብልጽግና እሳቤዎች ወደ ውጤት እየተቀየሩ መሆኑን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሀላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለጹ። በሲዳማ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ለትውልድ ቅርስ የሚሆኑና ነገን ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውም ተመላክቷል። አቶ አደም ፋራህ በሲዳማ ክልል ደራራና ሎካ አባያ ወረዳዎች እንዲሁም በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ቱላ ክፍለ ከተማ በፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ሙሉ ወጪ የተገነቡ የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤቶችን ዛሬ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።   በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ አቶ አደም ፋራህ እንዳሉት በፈተና አለመሸነፍ፣ በተግዳሮት አለመበገርና ፈተናን ወደ ዕድል ቀይሮ የስኬት ጉዞን የማስቀጠል የፓርቲው እሳቤዎች በውጤታማነት ተግባራዊ መሆን ጀምረዋል። ለዚህም የሲዳማ ክልል ማሳያ እንደሆነ በተግባር አይተናል ብለዋል። የሲዳማ ክልል በብልጽግና እሳቤዎች በመመራት ፈተናን ወደ ዕድል ከመቀየር ባለፈ ቤተሰብን ማዕከል ያደረገ ዕቅድ በማውጣት ለሌሎች ተሞክሮ የሚሆን ሥራ ሰርቷል ብለዋል። ፓርቲው በአጭር ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ እሳቤና የህዝብ ድጋፍ እንዳለው ገልጸው፣ "ይሄንን ማሳካት የሚቻለው በመንግስት አቅም ብቻ ሳይሆን የህዝብ አቅምን በመጠቀም ጭምር ነው” ብለዋል። በሲዳማ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችም ለትውልድ ቅርስ የሚሆኑና ነገን ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን በጉብኝት ወቅት መመልከታቸውን ገልጸዋል። በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ይህን ታሳቢ ያደረጉና በውጤታማነት እየተተገበሩ መሆናቸውን ገልጸው፣ አመራሩ ይህን ሥራ አጠናክሮ ማስቀጠል አለበት ሲሉ አሳስበዋል። በየደረጃው ያለው ህብረተሰብ ከብልጽግና ፓርቲ ጎን በመሆን ላበረከተው ሁለንተናዊ አስተዋጾ አመስግነው በቀጣይ ለሚሰሩ የልማት ሥራዎችም ከፓርቲው ጎን በመቆም ድጋፉን እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።   የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው እንዳሉት ሲዳማ ክልል ከሆነ በኋላ ባሉት ዓመታት የህዝብን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ መሰረተ ልማቶችን የማመሏት ስራዎች ተከናውነዋል። ለዚህም የህዝቡን የመንገድ ጥያቄ ለመመለስ ከ1 ሺህ 200 ኪሎ ሜትር በላይ አዲስ መንገድ በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቃ መደረጉን በማሳያነት ገልጸዋል። ከንጹህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት አንጻር ክልሉ ሲመሰረት 38 በመቶ የነበረውን ሽፋን በአሁኑ ወቅት 65 በመቶ ለማድረስ እንደተቻለም ጠቁመዋል። ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉና የቤተሰብ ብልጽግናን እውን የሚያደርጉ የሌማት ትሩፋትና ሌሎች መርሀ ግብሮችን ተግባራዊ በማድረግ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱንም አስረድተዋል። የክልሉን ህዝብ በማስተባበርና በማንቀሳቀስ ከ750 ሚሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን መገንባት እንደተቻለና በቀጣይም በህዝብ ተሳትፎ በርካታ የልማት ስራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ በበኩላቸው በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ከዛሬ ጀምሮ እየተመረቁ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች ወጪያቸው በፓርቲው አባላት፣ ደጋፊዎችና የተለያዩ አካላት ሙሉ ለሙሉ የተሸፈነ መሆኑን ተናግረዋል። "በዚህም 43 የፓርቲ ጽህፈት ቤቶች መገንባታቸውንና ለግንባታውም ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በጥሬና 200 ሺህ ብር በአይነት ለማሰባሰብ ተችሏል" ብለዋል። በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፣ በብልጽግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙን ጨምሮ ሌሎች የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችም ተገኝተዋል።  
የጋምቤላ ክልልን ሰላም በማጽናት የህዝቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ጥረት በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል- ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Sep 1, 2025 129
ጋምቤላ ፤ነሐሴ 26/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰላም በማጽናት የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ጥረት በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። በክልሉ አኮቦ ወረዳ ቀደም ሲል የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ በማቋቋም፤ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በጋምቤላ ከተማ ውይይት ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድሯ በክልሉ ያለውን ሰላም በማጽናት የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ጥረት በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል ። በክልሉ የተጀመሩ ልማት ስራዎችን በማፋጠን በህዝቡ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የሰላም አጀንዳ ዋነኛ ትኩረት መሆኑን አንስተው በተለይም በክልሉ ጠረፋማ ወረዳዎች ሰላምን በማጠናከር የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። የኮንፈረንሱ ዓላማም በወረዳው በታለመው የሰላም ግንባታና ልማት ዙሪያ የጠራ ግንዛቤ በመያዝ ለተግባራዊነቱ በጋራ ለመረባረብ በማሰብ ነው ብለዋል ።   የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር)፤ የህዝቡን አንድነትና አብሮነት በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ጠንክረንና ተባብረን መስራት ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል።
የሰላም ሰራዊት አባላት የከተማዋ ሰላም በማንኛውም እኩይ ተግባር የማይደፈርስ እንዲሆን አስችለዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Sep 1, 2025 178
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡- የሰላም ሰራዊት አባላት ከመላው የጸጥታ መዋቅር ጋር በመሆን የከተማዋ ሰላም በማንኛውም እኩይ ተግባር የማይደፈርስ እንዲሆን ማስቻላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በንድፈ ሀሳብና በተግባር ያሰለጠናቸውን የሰላም ሰራዊት አባላት አስመርቋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ሰላምን መጠበቅና ማጽናት የሁሉም ዜጋ ሀላፊነት ነው። የሰላም ሰራዊት አደረጃጀት ውጤታማ የሆነ የሰላም እሴት ግንባታ እንዲፈጠር ማስቻሉን ጠቁመዋል። የሰላም ሰራዊት አባላት ከመላው የጸጥታ መዋቅር ጋር በመሆን የከተማዋ ሰላም በማንኛውም እኩይ ተግባር የማይደፈርስ እንዲሆን ማስቻላቸውን አንስተዋል። የሰላም ሰራዊት አባላት ከጸጥታ አካላት ጋር ያከናወኑት ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸው፤ ይህንን ስራ ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የሰላም ሰራዊት አባላት በመዲናዋ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥና ልማት እንዲፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንም ተናግረዋል።   ተመራቂዎች የተጣለባቸውን ሃላፊነት በመገንዘብ ለመዲናዋ ሰላም በቁርጠኝነት እንዲሰሩም የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። ስራቸውንም ያለምንም አድልኦ በታማኝነት መወጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ከጸጥታ አካላት ጋር በቅርበት በመስራት የህዝቡን የሰላም እሴት ማዳበር ላይ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው አመላክተዋል። የአዲስ አበባ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው፤ ተመራቂዎች የንድፈ ሀሳብ እና የተግባር ስልጠናን ያጠናቀቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።   የሰላም ሰራዊት በከተማው የማያቋርጥ ልማት እንዲሳለጥ እንዲሁም አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ተናግረዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከመላው የጸጥታ መዋቅር ጋር በመተባበር ውጤታማ ስራ መሰራቱን ጠቁመዋል። የሰላም ሰራዊት ህዝቡ የሰላም ባለቤት እንዲሆን በማድረግ በኩልም ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። በቀጣዮቹ ጊዜያትም በመዲናዋ በርካታ ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሁነቶች እንደሚካሄዱ ገልጸዋል። የሰላም ሰራዊት አባላት ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ሁነቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ በጋራ እንደሚሰሩ አመልክተዋል። የሰላም ሰራዊት የከተማዋ ኩራት የሆነ የጸጥታ አደረጃጀት መሆኑን ጠቁመዋል። ከተመራቂዎች መካከል መስፍን አዱኛ እና ፊራኦል ደበላ በስልጠናው ባገኙት እውቀት መሰረት የተጣለባቸውን ሀላፊነት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።   ከጸጥታ አካላት ጋር በጋራ በመሆን የከተማዋን ሰላም ይበልጥ አስተማማኝ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።   በቀጣይ በመዲናዋ የሚከናወኑ ጉባኤዎች እና በዓላት በስኬት እንዲጠናቀቁ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልጸዋል።
በጋራ ትርክት ግንባታ፣ በሰላምና በልማት አጀንዳዎች ላይ በቅንጅት የተሰራው ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው- ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Sep 1, 2025 153
ሀዋሳ ፤ ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል በጋራ ትርክት ግንባታ፣ በሰላምና በልማት አጀንዳዎች ላይ በቅንጅት የተሰራው ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችና የመጡ ውጤቶችን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ከዘላቂ ሰላም ግንባታና የልማት ሥራዎችን ውጤታማ ከማድረግ አንፃር ብዙ ተሰርቶ ውጤቶችም መመዝገባቸውን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ ውጤቶቹም የህዝብ እገዛና የመንግስት ጥረት ታክሎበት የመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። የክልሉ ህዝብና መንግስት ለጋራ ትርክት ግንባታ፣ ለሰላምና የልማት አጀንዳዎች መሳካት በቅርበትና በትብብር መስራታቸው የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት አግዟል ብለዋል። በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት በማልማት የመጠቀም ጥረት፣ ለሰላምና የልማት አጀንዳዎች በጋራ በመትጋት በተለይም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ስኬት መመዝገቡን ለአብነት አንስተዋል። በፖለቲካው፣ በማህበራዊ ዘርፍና በምጣኔ ሃብት እድገት ረገድም በመንግስት የተያዙ ኢኒሼቲቮችን በመተግበርና ውጤታቸውን በመገምገም ድክመቶችን በማረም፤ ስኬቶችን ደግሞ አጠናክሮ በማስቀጠል ላይ እንገኛለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የብልጽግናን ግብ ለማሳካት የህዝቡን ኢኮኖሚያዊ አቅም መገንባት ያስፈልጋል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ያሉ አቅሞች ተለይተው ወደ ሥራ መገባቱን ጠቁመዋል። በክልሉ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የቱሪዝም መስህብ ስፍራዎችን በማስፋትና ለጎብኚዎች ምቹ በማድረግ፣ በገጠርና በከተሞች የኮሪደር ልማት፣ በኢንቨስትመንት እንዲሁም በሌማት ትሩፋት የሚታይ ተጨባጭ ለውጥና ውጤትም መምጣቱንም አብራርተዋል። የሲዳማ ክልል በሁሉም ዘርፍ ዕምቅ ጸጋ እንዳለው ያነሱት አቶ ደስታ ለዘላቂ ሰላምና ልማት የጋራ አቋም በመያዝ፣ የጋራ ትርክት በመገንባትና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማፅናት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት እንሰራለን ብለዋል። የተሻለ የጤና አገልግሎት፣ የመሰረተ ልማት፣ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋፋት ለላቀ ስኬት ለመብቃት እንተጋለን ሲሉም አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ ለልማት አጀንዳዎች ትኩረት በመስጠት፣ ሰላምን በማጽናትና አሰባሳቢ ትርክትን በመገንባት ለጋራ የብልጽግና ስኬት መትጋት የሁላችንም የጋራ አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት ሲሉም ተናግረዋል።
 ብልጽግና ፓርቲ በሀገሪቱ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት ባከናወናቸው ተግባራት ስኬት እያስመዘገበ  ነው
Sep 1, 2025 200
ሀዋሳ ፤ ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት በሀገሪቱ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት ባከናወናቸው ተግባራት ስኬት እያስመዘገበ መሆኑን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማእረግ የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማእከል ሀላፊ አቶ አደም ፋራህ አስታወቁ። አቶ አደም ፋራህ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የዳካ ክፍለ ከተማ የፓርቲውን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት መርቀው ስራ አስጀምረዋል።   አቶ አደም በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ እንዳሉት ብልጽግና ፓርቲ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ባሉት አመታት የህዝብንና የሀገሪቱን ብልጽግና ለማምጣት ያከናወናቸው ተግባራት ስኬታማ ናቸው። ለስኬቱ መላው አባሉና ደጋፊው ያለው ጥልቅ ፍቅር፣ የመደመር ፍልስፍናን ተከትሎ መስራት መቻሉ እና ለፓርቲው በትጋት ማገልገሉ እንደሆነ ተናግረዋል። የሲዳማ ህዝብ ለፓርቲው ባለው ዕምነትና ታማኝነት የሚወርዱ አቅጣጫዎችን በመቀበል በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ባደረገው ተሳትፎ ስራውን በግንባር ቀደምነት በመስራት ለሌሎች ምሳሌ መሆን እንደቻለ ገልጸዋል።   በሌሎች የልማት ስራዎችም በንቃት በመሳተፍ የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቁመው በኮሪደር ልማት ስራ ሀዋሳ ባላት ውበት ላይ ተጨማሪ ውበት ያላበሰ ስራ መሰራቱን ጠቅሰዋል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው ህዝቡ ለክልሉ ልማት በገንዘብ፣ በጉልበትና በዕውቀት የሚጠበቅበትን እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።   ፓርቲው የተመቸ ተቋም እንዲኖረው በተቀመጠ አቅጣጫ መሰረት የአባላትና የደጋፊዎቹን አቅም በመጠቀም ምቹ ጽህፈት ቤቶችን ገንብቶ ለአገልግሎት ማብቃቱን ተናግረዋል። የፓርቲው የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ እንዳሉት የተገነባው ባለ አራት ወለል ህንጻ ለስራ ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው።   በክልሉ ተግባራዊ በተደረገው የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር በርካቶች እየተለወጡ መሆኑንም ገልጸዋል። በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፣ በብልጽግና ፓርቲ የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ፖለቲካ
የምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎችን የሰላም እሴቶች ግንባታ ይበልጥ ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቷል
Sep 2, 2025 72
ድሬደዋ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፡-የምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎችን የሰላም እሴቶችን ግንባታ ይበልጥ ለማጠናከር ትኩረት መሰጠቱ ተገልጿል። የምስራቅ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎችን የሰላም እሴቶችን ግንባታና ግንኙነትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል የምክክር መድረክ በድሬደዋ እየተካሄደ ነው። የምክክር መድረኩን የፌደሬሽን ምክር ቤት ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ነው። የፌደሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዘሐራ ሁመድ እና የሰላም ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። በተጨማሪም የምስራቅ ተጎራባች ክልሎች የሆኑት የሶማሌ፣ የአፋር፣ የሐረሪ፣ የምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ኦሮሚያ ዞኖችና የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች እንዲሁም የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች እየተሳተፉ ነው። በቀጠናው ያለውን ዘላቂ ሰላም ለማፅናት እና የተጎራባች ክልሎቹን የመንግስታት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ መድረክ መሆኑን የፌደሬሽን ምክር ቤት የህዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ሞገስ ጀምበሬ ለኢዜአ ገልጸዋል። እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ፥ ተጎራባች ክልሎቹ የፈጠሩትን የጋራ ፎረም በማጎልበት በአካባቢው ተቀናጅተው የጀመሩትን የብልፅግና ጉዞ ለማጠናከር ያግዛቸዋል።
የህዳሴ ግድብ የአባይን የዘመናት ህልም ወደ ፍሬ ማፍራት እንዲሸጋገር አድርጓል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 1, 2025 234
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአባይን የዘመናት ህልም እና እንጉርጉሮ ወደ ሚጨበጥ ውጤት እንዲቀየር ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የ“ኩስመና ታሪክ ማብቂያ” በሚል ርዕስ የጉባ ላይ ወግ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያውያን ለበርካታ መቶ ዓመታት በአባይ ወንዝ ተጠቅሞ ለማደግ ፍላጎቶች እንደነበሯቸው እና ሙከራዎችን እንዳደረጉ አመልክተዋል። ሙከራዎቹ በገንዘብ እጥረት፣በቴክኒክ አቅም ውስንነት፣ የጂኦ ፖለቲካ አለመመቸት እና ብዙ ምክንያቶች ሙከራዎቹን እንዳይሳኩ ማድረጉን ተናግረዋል። አባይን አስመልክቶ ያሉ በርካታ ስነ ጽሁፎች፣ ግጥሞች፣ ዘፈኖች እና እንጉርጉሮዎች በሀብቱ መጠቀምን ሳይሆን ባለመጠቀም ውስጥ ያለን ቁጭት አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። በወንዙ ሀብት ተጠቅሞ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግንባታ ማከናወን የተቻለው ከጂኦ ፖለቲካዊ ኩስመና ወደ ተሻለ ቁመና ሽግግር ውጤት መሆኑን ነው የገለጹት። መንግስት ጂኦ ፖለቲካዊ ኩስመና በፍጹም አንቀበልም እኛን አይመጥነንም፣ ኢትዮጵያ ካላት ስፋት አንጻር ለህዝቡ ታሪክ የሚበጅ አይደለም በማለት ትርክቱን ለመቀየር ወደ ስራ መግባቱን አመልክተዋል። በጂኦ ፖለቲክሱ የተሻለ ቁመናን ለመያዝ እየተከናወነ ባለው ስራ እና ሌሎች አስቻይ ሁኔታዎች ምክንያት የዘመናት ህልም፣የዘመናት እንጉርጉሮና የዘመናት ለቅሶ ወደ ፍሬና ወደ ውጤት እንዲቀየር ማስቻሉን ተናግረዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #Ethiopia #ኢትዮጵያ #ህዳሴ #የአባይግድብ
ሕዳሴን እንደ መደበኛ ፕሮጀክት ሳይሆን እንደ የዘመናት ቀንበር መስበሪያ፤እንደ የታሪክ መታጠፊያ መስመር አድርጌ ነው የማየው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 1, 2025 157
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዳሴ ግድብን እንደ መደበኛ ፕሮጀክት ሳይሆን የዘመናት ቀንበር መስበሪያ፤የታሪክ መታጠፊያ መስመር አድርጌ ነው የማየው አሉ። "የኩስመና ታሪክ ማብቂያ" በሚል ርዕስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ጋር ባደረጉት የጉባ ላይ ወግ፤ከሕዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ክትትልና ስኬታማ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ ገለጻ አድርገዋል። በገለጻቸውም፤አንድን ሥራ ጀምሮ ለመጨረስ፤በቅድሚያ ጨርሶ የማየት ዐቅም ያስፈልጋል ብለዋል። ያንን ቀድመን ጨርሰን ያየነውን ነገር በርካቶች እንዲያዩት ደግሞ በከፍተኛ ዲሲፕሊን መትጋት ይፈልጋል ነው ያሉት። በዚሁ መሠረት ላለፉት ሰባት ዓመታት ወደ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በመመላለስ በንቃት ክትትል ማድረጋቸውን አንስተዋል። የክትትል ሥራ ለማንኛውም የሥራ መሥክ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤የተጉ እናቶች ልጆጃቸውን ለፍሬ እንዳበቁ ሁሉ፤ የተጉ ሠራተኞች ደግሞ ሀገራቸውን ለፍሬ አብቅተዋል፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እየሆነ ያለውም ይህ ነው ብለዋል። የሕዳሴ ግድብን እንደ መደበኛ ፕሮጀክት ሳይሆን የዘመናት ቀንበር መስበሪያ፤ የታሪክ መታጠፊያ መስመር አድርጌ ነው የማየው ሲሉም ገልጸዋል። እንደሚታወቀው ዓባይ ለዘመናት ሲሄድብን ኖሯል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የሕዳሴ እሳቤ ውኃ እንዲሄድብን ሳይሆን ጀልባ ሠርተን እኛ በውኃ ላይ እንድንሄድበት ነው፤በዚህም ዓሣ ማጥመድ እንድንችል ነው፤ ያስቀረነውን አፈር መርምረን ወርቅ ይኑረው ወይም አይኑረው መለየት እንድንችል ነው ሲሉ አብራርተዋል። ዓባይን ጨርሶ ኢትዮጵያ ውስጥ የታሪክ እጥፋት ማረጋገጥ የመጨረሻ ጸሎቴና ምኞቴ ነበር ሲሉም ገልጸዋል። ሲጀመር ፈጣሪ ትልቁን ዓባይ ለኢትዮጵያ አምኖ የሰጠው በፍትሐዊነት እንደምትጠቀመው ስላመነባት ነው ብዬ አምናለሁ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። በዚህ አግባብ ነው ግድባችንን ለፍሬ ያበቃነው፤በሱዳንም ሆነ በግብጽ ያሉ ግድቦች አንድም ሊትር አልቀነሱም በቂ መረጃ አለን፤ ወደ ፊትም እንዳይቀንሱ ነው የእኛ ፍላጎት በዚሁ አግባብ እንሠራለን ብለዋል። ከተደመርን እና ከተጋን ያሰብነው ይሳካል፥ ለዚህም የሕዳሴው ግድብ ማሳያ ነው በማለት ጠቅሰዋል። #Ethiopian_News_Agency #Ethiopia #ኢትዮጵያ #ኢዜአ
የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በፅናት በማለፍና ወደ ዕድል በመቀየር የብልጽግና እሳቤዎች ወደ ውጤት እየተቀየሩ ነው- አቶ አደም ፋራህ
Sep 1, 2025 135
ሀዋሳ ፤ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ) ፡-የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በፅናት በማለፍና ወደ ዕድል በመቀየር የብልጽግና እሳቤዎች ወደ ውጤት እየተቀየሩ መሆኑን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሀላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለጹ። በሲዳማ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ለትውልድ ቅርስ የሚሆኑና ነገን ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውም ተመላክቷል። አቶ አደም ፋራህ በሲዳማ ክልል ደራራና ሎካ አባያ ወረዳዎች እንዲሁም በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ቱላ ክፍለ ከተማ በፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ሙሉ ወጪ የተገነቡ የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤቶችን ዛሬ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።   በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ አቶ አደም ፋራህ እንዳሉት በፈተና አለመሸነፍ፣ በተግዳሮት አለመበገርና ፈተናን ወደ ዕድል ቀይሮ የስኬት ጉዞን የማስቀጠል የፓርቲው እሳቤዎች በውጤታማነት ተግባራዊ መሆን ጀምረዋል። ለዚህም የሲዳማ ክልል ማሳያ እንደሆነ በተግባር አይተናል ብለዋል። የሲዳማ ክልል በብልጽግና እሳቤዎች በመመራት ፈተናን ወደ ዕድል ከመቀየር ባለፈ ቤተሰብን ማዕከል ያደረገ ዕቅድ በማውጣት ለሌሎች ተሞክሮ የሚሆን ሥራ ሰርቷል ብለዋል። ፓርቲው በአጭር ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ እሳቤና የህዝብ ድጋፍ እንዳለው ገልጸው፣ "ይሄንን ማሳካት የሚቻለው በመንግስት አቅም ብቻ ሳይሆን የህዝብ አቅምን በመጠቀም ጭምር ነው” ብለዋል። በሲዳማ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችም ለትውልድ ቅርስ የሚሆኑና ነገን ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን በጉብኝት ወቅት መመልከታቸውን ገልጸዋል። በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ይህን ታሳቢ ያደረጉና በውጤታማነት እየተተገበሩ መሆናቸውን ገልጸው፣ አመራሩ ይህን ሥራ አጠናክሮ ማስቀጠል አለበት ሲሉ አሳስበዋል። በየደረጃው ያለው ህብረተሰብ ከብልጽግና ፓርቲ ጎን በመሆን ላበረከተው ሁለንተናዊ አስተዋጾ አመስግነው በቀጣይ ለሚሰሩ የልማት ሥራዎችም ከፓርቲው ጎን በመቆም ድጋፉን እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።   የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው እንዳሉት ሲዳማ ክልል ከሆነ በኋላ ባሉት ዓመታት የህዝብን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ መሰረተ ልማቶችን የማመሏት ስራዎች ተከናውነዋል። ለዚህም የህዝቡን የመንገድ ጥያቄ ለመመለስ ከ1 ሺህ 200 ኪሎ ሜትር በላይ አዲስ መንገድ በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቃ መደረጉን በማሳያነት ገልጸዋል። ከንጹህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት አንጻር ክልሉ ሲመሰረት 38 በመቶ የነበረውን ሽፋን በአሁኑ ወቅት 65 በመቶ ለማድረስ እንደተቻለም ጠቁመዋል። ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉና የቤተሰብ ብልጽግናን እውን የሚያደርጉ የሌማት ትሩፋትና ሌሎች መርሀ ግብሮችን ተግባራዊ በማድረግ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱንም አስረድተዋል። የክልሉን ህዝብ በማስተባበርና በማንቀሳቀስ ከ750 ሚሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን መገንባት እንደተቻለና በቀጣይም በህዝብ ተሳትፎ በርካታ የልማት ስራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ በበኩላቸው በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ከዛሬ ጀምሮ እየተመረቁ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች ወጪያቸው በፓርቲው አባላት፣ ደጋፊዎችና የተለያዩ አካላት ሙሉ ለሙሉ የተሸፈነ መሆኑን ተናግረዋል። "በዚህም 43 የፓርቲ ጽህፈት ቤቶች መገንባታቸውንና ለግንባታውም ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በጥሬና 200 ሺህ ብር በአይነት ለማሰባሰብ ተችሏል" ብለዋል። በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፣ በብልጽግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙን ጨምሮ ሌሎች የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችም ተገኝተዋል።  
የጋምቤላ ክልልን ሰላም በማጽናት የህዝቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ጥረት በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል- ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Sep 1, 2025 129
ጋምቤላ ፤ነሐሴ 26/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰላም በማጽናት የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ጥረት በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። በክልሉ አኮቦ ወረዳ ቀደም ሲል የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ በማቋቋም፤ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በጋምቤላ ከተማ ውይይት ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድሯ በክልሉ ያለውን ሰላም በማጽናት የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ጥረት በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል ። በክልሉ የተጀመሩ ልማት ስራዎችን በማፋጠን በህዝቡ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የሰላም አጀንዳ ዋነኛ ትኩረት መሆኑን አንስተው በተለይም በክልሉ ጠረፋማ ወረዳዎች ሰላምን በማጠናከር የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። የኮንፈረንሱ ዓላማም በወረዳው በታለመው የሰላም ግንባታና ልማት ዙሪያ የጠራ ግንዛቤ በመያዝ ለተግባራዊነቱ በጋራ ለመረባረብ በማሰብ ነው ብለዋል ።   የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር)፤ የህዝቡን አንድነትና አብሮነት በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ጠንክረንና ተባብረን መስራት ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል።
የሰላም ሰራዊት አባላት የከተማዋ ሰላም በማንኛውም እኩይ ተግባር የማይደፈርስ እንዲሆን አስችለዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Sep 1, 2025 178
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡- የሰላም ሰራዊት አባላት ከመላው የጸጥታ መዋቅር ጋር በመሆን የከተማዋ ሰላም በማንኛውም እኩይ ተግባር የማይደፈርስ እንዲሆን ማስቻላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በንድፈ ሀሳብና በተግባር ያሰለጠናቸውን የሰላም ሰራዊት አባላት አስመርቋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ሰላምን መጠበቅና ማጽናት የሁሉም ዜጋ ሀላፊነት ነው። የሰላም ሰራዊት አደረጃጀት ውጤታማ የሆነ የሰላም እሴት ግንባታ እንዲፈጠር ማስቻሉን ጠቁመዋል። የሰላም ሰራዊት አባላት ከመላው የጸጥታ መዋቅር ጋር በመሆን የከተማዋ ሰላም በማንኛውም እኩይ ተግባር የማይደፈርስ እንዲሆን ማስቻላቸውን አንስተዋል። የሰላም ሰራዊት አባላት ከጸጥታ አካላት ጋር ያከናወኑት ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸው፤ ይህንን ስራ ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የሰላም ሰራዊት አባላት በመዲናዋ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥና ልማት እንዲፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንም ተናግረዋል።   ተመራቂዎች የተጣለባቸውን ሃላፊነት በመገንዘብ ለመዲናዋ ሰላም በቁርጠኝነት እንዲሰሩም የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። ስራቸውንም ያለምንም አድልኦ በታማኝነት መወጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ከጸጥታ አካላት ጋር በቅርበት በመስራት የህዝቡን የሰላም እሴት ማዳበር ላይ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው አመላክተዋል። የአዲስ አበባ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው፤ ተመራቂዎች የንድፈ ሀሳብ እና የተግባር ስልጠናን ያጠናቀቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።   የሰላም ሰራዊት በከተማው የማያቋርጥ ልማት እንዲሳለጥ እንዲሁም አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ተናግረዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከመላው የጸጥታ መዋቅር ጋር በመተባበር ውጤታማ ስራ መሰራቱን ጠቁመዋል። የሰላም ሰራዊት ህዝቡ የሰላም ባለቤት እንዲሆን በማድረግ በኩልም ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። በቀጣዮቹ ጊዜያትም በመዲናዋ በርካታ ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሁነቶች እንደሚካሄዱ ገልጸዋል። የሰላም ሰራዊት አባላት ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ሁነቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ በጋራ እንደሚሰሩ አመልክተዋል። የሰላም ሰራዊት የከተማዋ ኩራት የሆነ የጸጥታ አደረጃጀት መሆኑን ጠቁመዋል። ከተመራቂዎች መካከል መስፍን አዱኛ እና ፊራኦል ደበላ በስልጠናው ባገኙት እውቀት መሰረት የተጣለባቸውን ሀላፊነት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።   ከጸጥታ አካላት ጋር በጋራ በመሆን የከተማዋን ሰላም ይበልጥ አስተማማኝ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።   በቀጣይ በመዲናዋ የሚከናወኑ ጉባኤዎች እና በዓላት በስኬት እንዲጠናቀቁ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልጸዋል።
በጋራ ትርክት ግንባታ፣ በሰላምና በልማት አጀንዳዎች ላይ በቅንጅት የተሰራው ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው- ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Sep 1, 2025 153
ሀዋሳ ፤ ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል በጋራ ትርክት ግንባታ፣ በሰላምና በልማት አጀንዳዎች ላይ በቅንጅት የተሰራው ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችና የመጡ ውጤቶችን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ከዘላቂ ሰላም ግንባታና የልማት ሥራዎችን ውጤታማ ከማድረግ አንፃር ብዙ ተሰርቶ ውጤቶችም መመዝገባቸውን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ ውጤቶቹም የህዝብ እገዛና የመንግስት ጥረት ታክሎበት የመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። የክልሉ ህዝብና መንግስት ለጋራ ትርክት ግንባታ፣ ለሰላምና የልማት አጀንዳዎች መሳካት በቅርበትና በትብብር መስራታቸው የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት አግዟል ብለዋል። በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት በማልማት የመጠቀም ጥረት፣ ለሰላምና የልማት አጀንዳዎች በጋራ በመትጋት በተለይም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ስኬት መመዝገቡን ለአብነት አንስተዋል። በፖለቲካው፣ በማህበራዊ ዘርፍና በምጣኔ ሃብት እድገት ረገድም በመንግስት የተያዙ ኢኒሼቲቮችን በመተግበርና ውጤታቸውን በመገምገም ድክመቶችን በማረም፤ ስኬቶችን ደግሞ አጠናክሮ በማስቀጠል ላይ እንገኛለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የብልጽግናን ግብ ለማሳካት የህዝቡን ኢኮኖሚያዊ አቅም መገንባት ያስፈልጋል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ያሉ አቅሞች ተለይተው ወደ ሥራ መገባቱን ጠቁመዋል። በክልሉ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የቱሪዝም መስህብ ስፍራዎችን በማስፋትና ለጎብኚዎች ምቹ በማድረግ፣ በገጠርና በከተሞች የኮሪደር ልማት፣ በኢንቨስትመንት እንዲሁም በሌማት ትሩፋት የሚታይ ተጨባጭ ለውጥና ውጤትም መምጣቱንም አብራርተዋል። የሲዳማ ክልል በሁሉም ዘርፍ ዕምቅ ጸጋ እንዳለው ያነሱት አቶ ደስታ ለዘላቂ ሰላምና ልማት የጋራ አቋም በመያዝ፣ የጋራ ትርክት በመገንባትና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማፅናት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት እንሰራለን ብለዋል። የተሻለ የጤና አገልግሎት፣ የመሰረተ ልማት፣ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋፋት ለላቀ ስኬት ለመብቃት እንተጋለን ሲሉም አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ ለልማት አጀንዳዎች ትኩረት በመስጠት፣ ሰላምን በማጽናትና አሰባሳቢ ትርክትን በመገንባት ለጋራ የብልጽግና ስኬት መትጋት የሁላችንም የጋራ አጀንዳ ሆኖ መቀጠል አለበት ሲሉም ተናግረዋል።
 ብልጽግና ፓርቲ በሀገሪቱ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት ባከናወናቸው ተግባራት ስኬት እያስመዘገበ  ነው
Sep 1, 2025 200
ሀዋሳ ፤ ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት በሀገሪቱ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት ባከናወናቸው ተግባራት ስኬት እያስመዘገበ መሆኑን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማእረግ የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማእከል ሀላፊ አቶ አደም ፋራህ አስታወቁ። አቶ አደም ፋራህ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የዳካ ክፍለ ከተማ የፓርቲውን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት መርቀው ስራ አስጀምረዋል።   አቶ አደም በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ እንዳሉት ብልጽግና ፓርቲ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ባሉት አመታት የህዝብንና የሀገሪቱን ብልጽግና ለማምጣት ያከናወናቸው ተግባራት ስኬታማ ናቸው። ለስኬቱ መላው አባሉና ደጋፊው ያለው ጥልቅ ፍቅር፣ የመደመር ፍልስፍናን ተከትሎ መስራት መቻሉ እና ለፓርቲው በትጋት ማገልገሉ እንደሆነ ተናግረዋል። የሲዳማ ህዝብ ለፓርቲው ባለው ዕምነትና ታማኝነት የሚወርዱ አቅጣጫዎችን በመቀበል በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ባደረገው ተሳትፎ ስራውን በግንባር ቀደምነት በመስራት ለሌሎች ምሳሌ መሆን እንደቻለ ገልጸዋል።   በሌሎች የልማት ስራዎችም በንቃት በመሳተፍ የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቁመው በኮሪደር ልማት ስራ ሀዋሳ ባላት ውበት ላይ ተጨማሪ ውበት ያላበሰ ስራ መሰራቱን ጠቅሰዋል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው ህዝቡ ለክልሉ ልማት በገንዘብ፣ በጉልበትና በዕውቀት የሚጠበቅበትን እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።   ፓርቲው የተመቸ ተቋም እንዲኖረው በተቀመጠ አቅጣጫ መሰረት የአባላትና የደጋፊዎቹን አቅም በመጠቀም ምቹ ጽህፈት ቤቶችን ገንብቶ ለአገልግሎት ማብቃቱን ተናግረዋል። የፓርቲው የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ እንዳሉት የተገነባው ባለ አራት ወለል ህንጻ ለስራ ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው።   በክልሉ ተግባራዊ በተደረገው የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር በርካቶች እየተለወጡ መሆኑንም ገልጸዋል። በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፣ በብልጽግና ፓርቲ የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ማህበራዊ
የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን የተሰጠውን አገር የማስተዋወቅ ተልዕኮ በስኬት አጠናቆ ተመልሷል-ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን
Sep 2, 2025 21
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን የተሰጠውን አገር የማስተዋወቅ ተልዕኮ በስኬት አጠናቆ ተመልሷል ሲሉ የመከላከያ ሠራዊት ስነልቦና ግንባታ ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን ገለጹ። በሩሲያ ሞስኮ በተዘጋጀው የማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብቷል።   ማርቺንግ ባንዱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፈያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። የመከላከያ ሠራዊት ስነልቦና ግንባታ ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን በወቅቱ፣ የማርችንግ ባንድ ቡድኑ አባላት ተልዕኳቸውን በአግባቡ ያሳኩ የሀገር ጀግኖች መሆናቸውን ተናግረዋል። በዓለም አቀፍ መድረክ ኢትዮጵያን በአግባቡ በማስተዋወቅ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እና ሀገርን ያኮራ ተግባር ማከናወናቸውን በመጥቀስ፥ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል። የሀገር ኩራት መሆኑን ከዚህ ቀደም በብዙ ሥራዎቹ ያስመሰከረው የመከላከያ ማርችንግ ባንድ፥ በፌስቲቫሉ ላይ ያሳየው ሙያዊ ዲሲፒሊን ለዓለም አብነት የሚሆን ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ሩሲያ ባዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የመከላከያ ማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ መሳተፏ ወታደራዊ የልምድ ልውውጥ ለማድረግና ትብብርን ለማጠናከር ጉልህ አበርክቶ መጫወቱን ተናግረዋል።   የመከላከያ ኪነ-ጥበባት ሥራዎች ዳይሬክተር ኮሎኔል ማንያህለዋል ታደለ ዝግጅቱ የተሳካ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከአፍሪካ፣ ከአውሮፓ እና ከኤስያ የተወጣጡ የበርካታ ሀገራት የማርችንግ ባንድ አባላት መሳተፋቸውን ተናግረዋል። ዘመናዊ የሙዚቃ መሳሪያን ተጠቅመን ባህላዊ ዘፈኖቻችንን እና ባህላዊ ጭፈራዎቻችንን አዋህደን በማቅረብ ዓለምን ያስደነቀ ሥራ ሠርተናል ብለዋል።   የማርችንግ ባንዱ ሉዑክ አባል የሆነችው ሻምበል ሔለን አለሙ፤ መድረኩ ልምዳችን ያካፈልንበት እና ከእነሱም ልምድ የወሰድንበት ነበር ብላለች፡፡ ሌላኛዋ የባንዱ ሉዑክ አባል ሐምሳ አለቃ ሒወት አሰፋ፤ ፌሰቲባሉ የአገራችን ባህልና ወግ ለአለም ከማስተዋወቅ ባሻገር ሩሲያውያን በአገራቸው ጉዳይ በአንድ ልብ መካሪ በአንድ ቃል ተናጋሪ መሆናቸውን አይተናል ብላለች።      
የጳጉሜን ቀናት በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማክበር ዝግጅት ተደርጓል-የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Sep 2, 2025 43
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፦የ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት ዋዜማ አምስቱ የጳጉሜን ቀናት በሀገር ዓቀፍ ደረጃ በተለያየ ዝግጅትና ስያሜ ለማክበር የዝግጅት ስራ መጠናቀቁን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል። ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት፥ የ2018 ዓ.ም የአዲስ ዓመት ዋዜማ አምስቱ የጳጉሜን ወር ቀናት አከባበር ዝግጅትና ስያሜን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ በ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት መሸጋገሪያ አምስት የጳጉሜን ቀናትም በተለያዩ ዝግጅቶች ለማክበር ዝግጅት መደረጉን አመልክተዋል። በዚህም ጳጉሜን 1 የጽናት ቀን፣ጳጉሜን 2 የህብር ቀን፣ ጳጉሜን 3 የእምርታ ቀን፣ ጳጉሜን 4 የማንሰራራት ቀን እና ጳጉሜን 5 የነገው ቀን በሚል እንደሚከበሩ ገልጸዋል። ቀናቱም በሀገር ዓቀፍ ደረጃ በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች እንደሚከበሩ ጠቁመዋል።
የመከላከያ ማርችንግ ባንድ በሩሲያ ቆይታው የሀገርን ባህል እና ሙያዊ ብቃቱን ለዓለም በማስተዋወቅ አኩሪ ተግባር ፈጽሟል-ሜጀር ጀነራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን
Sep 2, 2025 78
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017 (ኢዜአ)፦የመከላከያ ማርችንግ ባንድ ሩሲያ ባዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ የሀገርን ባህልና ገፅታ እና ሙያዊ ብቃቱን ለዓለም በማስተዋወቅ አኩሪ ተግባር መፈጸሙን የመከላከያ ሠራዊት ስነልቦና ግንባታ ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን ገለጹ። በሩሲያ ሞስኮ በተዘጋጀው የማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ መከላከያ ማርችንግ ባንድ ቡድን ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብቷል።   ማርቺንግ ባንዱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። የመከላከያ ሠራዊት የስነልቦና ግንባታ ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን በዚሁ ወቅት፣የማርችንግ ባንድ ቡድኑ አባላት ተልዕኳቸውን በአግባቡ ያሳኩ የሀገር ጀግኖች መሆናቸውን ተናግረዋል። በዓለም አቀፍ መድረክ ኢትዮጵያን በአግባቡ በማስተዋወቅ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እና ሀገርን ያኮራ ተግባር ማከናወናቸውን በመጥቀስ፥ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል። የሀገር ኩራት መሆኑን ከዚህ ቀደም በብዙ ሥራዎቹ ያስመሰከረው የመከላከያ ማርችንግ ባንድ፥ በፌስቲቫሉ ላይ ያሳየው ሙያዊ ዲሲፕሊን ለዓለም አብነት የሚሆን ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ሩሲያ ለ5 ቀናት ባዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የመከላከያ ማርችንግ ባንድ ፌስቲቫል ላይ መሳተፏ ወታደራዊ የልምድ ልውውጥ ለማድረግና ትብብርን ለማጠናከር ጉልህ አበርክቶ መጫወቱን ተናግረዋል። የመከላከያ ኪነ- ጥበባት ሥራዎች ዳይሬክተር ኮሎኔል ማንያህለዋል ታደለ ዝግጅቱ የተሳካ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከአፍሪካ፣ከአውሮፓ እና ከእስያ የተወጣጡ የበርካታ ሀገራት የማርችንግ ባንዶች የተሳተፉበት መሆኑን ተናግረዋል። ዘመናዊ የሙዚቃ መሳሪያን ተጠቅመን ባህላዊ ዘፈኖቻችንን እና ባህላዊ ጭፈራዎቻችንን አዋህደን በማቅረብ ዓለምን ያስደነቀ ሥራ ሠርተናል ብለዋል። የማርችንግ ባንዱ ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ዘመቻ በዲ በበኩላቸው፥ ቡድኑ በሠራቸው የሙዚቃ ሥራዎች እና የመድረክ ላይ እንቅስቃሴዎቹ ከፍተኛ አድናቆት ማግኘቱን ገልፀዋል። ቡድኑ የሀገራችንን ብሔሮች ብሔረሰቦች አለባበስ፣ ዜማ፣ ውዝዋዜና ሌሎች የጥበብ ባህሎች በማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።  
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ ያለው ሐይቅ ስያሜ “ንጋት” ብለነዋል
Sep 2, 2025 114
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017 (ኢዜአ)፡-በታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ ያለው ሐይቅ ስሜ “ንጋት” እንዲባል መወሰኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ። "የኩስመና ታሪክ ማብቂያ" በሚል ርዕስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባደረጉት የጉባ ላይ ወግ፤ በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ላይ ያለው ሐይቅ በኢትዮጵያ ትልቁ ነው፤በአፍሪካም ከትላልቆቹ ሐይቆች አንዱ ነው ብለዋል። አሁን ላይም 74 ትሪሊየን ሊትር ውኃ መያዙን ጠቅሰው፤ በሕዳሴው ግድብ ያለውን ሐይቅ ከእንቅልፍ የነቃንበት ዘመን በመሆኑና ስያሜው የወል እንዲሆን በማሰብ “ንጋት” ብለነዋል ሲሉ አስታውቀዋል። ንጋት ማለት ረዥሙ ጨለማ አልቆ ጎኅ ሲቀድ፣ የብርሃን ፍንጣቂ መታየት ሲጀምር ያለው ጊዜ መሆኑንም አስረድተዋል። ንጋት ከፊታችን ብርሃን መምጣት ያሳያል፤የውሏችን እንቅስቃሴ የሚጀመርበት ጊዜም ነው ብለዋል። ያለንበት ወቅት የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን መሆኑን እኛ ብቻ ሳንሆን ዓለም ከዓባይ ጋር የሚመሰክረው ነው ብለዋል።
ኢኮኖሚ
በምስራቅ ሸዋ ዞን ከ80 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በቦሎቄ ልማት ተሸፍኗል
Sep 2, 2025 7
አዳማ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፦በምስራቅ ሸዋ ዞን በኩታ ገጠም የሚለማ ከ80 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በኤክስፖርት ቦሎቄ መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። ዞኑ ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቦሎቄ ምርት ለማግኘት በትኩረት እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል። የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገዬ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ አብዛኞቹ የዞኑ ወረዳዎች ለቆላ ጥራጥሬ ሰብሎች አመቺ መሆናቸውን ገልጸዋል። በዞኑ የግብርና የኤክስፖርት ምርቶች ላይ በትኩረት እየሰራን ነው ያሉት አቶ አብነት በተለይ የቦሎቄና የማሾ ሰብሎች በሰፊው እንደሚመረቱ ተናግረዋል። በዚህም የዞኑ አርሶ አደሮች በማህበር ተደራጅተው በቦሎቄ ልማት ላይ በብዛት እንዲሳተፉ የማድረግ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። በዚህም በዞኑ ከ80 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም በኤክስፖርት ቦሎቄ ልማት መሸፈኑን ተናግረዋል። አዳሚ ቱሉ፣ ጂዱ ኮሞቦልቻ፣ ቦሰት፣ ሎሜ፣ ፈንታሌ፣ ዱግዳና ቦራ ወረዳዎች የቦሎቄ ልማት በኩታገጠም በስፋት የለማባቸው ወረዳዎች መሆናቸው ተናግረዋል።
2017 ዓ.ም ውስብስብ ፈተናዎችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪ ድሎች የተመዘገቡበት ነበር-ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር)
Sep 2, 2025 27
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017 (ኢዜአ)፡- 2017 የበጀት ዓመት ውስብስብ ፈተናዎችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪና እመርታዊ ድሎች የተመዘገቡበት እንደነበር የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሰጡት መግለጫ፤ የተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ለኢትዮጵያ በእጅጉ ስኬታማ ዓመት መሆኑን አስታውቀዋል። ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) አክለውም፥ 2017 የበጀት ዓመት ውስብስብ ፈተናዎችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪና እመርታዊ ድሎች የተመዘገቡበት ነበር ብለዋል። ድሎቹ ብዙ ሊነገርላቸው የሚገባ፣ትምህርትም የሚቀሰምባቸው እንዲሁም ለቀጣይ ሀገራዊ ድሎች እንደወረት የሚወሰዱ መሆናቸውን ጠቁመዋል። መጪው አዲስ ዓመትም እነዚህን ድሎች በይበልጥ የምናሰፋበት ብሎም ተግዳሮቶቻችንን የምንቀንስበት እንዲሆን ሰፊ ዕቅድ ተቀምጧል ሲሉ አመላክተዋል። ይህን መሠረት በማድረግም ወደ ንቅናቄ መገባቱን ነው የተናገሩት። የጳጉሜን ወር ወደ አዲሱ ዓመት የምንሸጋገርበት ድልድይ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ቀናቱ በተለይም ለኢትዮጵያውያን በእጅጉ ልዩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣዮቹ የጳጉሜን ቀናት በሀገር አቀፍ ደረጃ በተናበበ አካሄድ እንደሚከበሩም ጠቁመዋል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ሀሳቡን የሚያጋራበት የአጭር መልዕክት ማስተላለፊያ ኮድ ይፋ ሆነ
Sep 2, 2025 55
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017 (ኢዜአ)፦ከዛሬ ጀምሮ ለ33 ቀናት የሚቆይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን በተመለከተ ያለውን ሃሳብና መልዕክት የሚያጋራበት 8120 አጭር መልዕክት ማስተላለፊያ ኮድ ይፋ ሆኗል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር ዜጎች መልካም ምኞታቸውን የሚገልጹበት "የትውልድ አሻራ ዲጂታል የብስራት መልዕክትና ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት" በሚል ስያሜ መልዕክት እንዲያስተላልፉ የሚያስችል ነው።   በዚህ ወቅት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) እንዳሉት፥ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የወል ትርክታችንና ላባችንን ቀለም ክንዳችንን ደግሞ እንደብዕር አድርገን የፃፍነው መፅሀፍ ነው። ሕዳሴ ግድብ ከተባበርን የዕድገት ማማ ላይ መውጣት እንደምንችል ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። ህብረተሰቡ ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ የበኩሉን ሲወጣ መቆየቱን ጠቁመው፤ ኢትዮ ቴሌኮም በ"8100 A" ላይ በመላክ በተከታታይ ለሶስት ዙር የድጋፍ ማሰባሰብ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። ከዛሬ ጀምሮ ህብረተሰቡ ደስታውንና ስሜቱን የሚያጋራበት 8120 በእጅ ስልክ በመላክ መልዕክት ማጋራት ይችላል ነው ያሉት። የአጭር መልዕክት ማስተላለፊያ ኮዱ ከዛሬ ነሃሴ 27 ቀን 2017 እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 ድረስ ባሉት ጊዜያት ህብረተሰቡ ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን መሆን ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ በተመለከተ በአጭር መልዕክት ሃሳቡን በመግለፅ አሻራውን ለታሪክ መዘክርነት ማስቀመጥ የሚችልበት ነው። በአጭር መልዕክት ማስተላለፊያ ኮዱ 1 ቁጥር መላክ አምስት ብር ድጋፍ ማድረግና በህብረት ችለናል የሚል መልዕክት ያለው ሲሆን፤ 2 ቁጥር ደግሞ የ10 ብር ድጋፍና ታላቁ ሕዳሴ ግድብ የብልፅግና አሻራ የሚል መልዕክት ያለው መሆኑ ተገልጿል። 3 ቁጥር የ15 ብር ድጋፍና ግድባችን የአሸናፊነት ድል አክሊል እንዲሁም 4 ቁጥር የ100 ብር ድጋፍና ግድባችን የአባይ ዘመን ትውልድ የተጋድሎ ሰንደቅ የሚል መልዕክት ያላቸው መሆኑ ተጠቁሟል። በተጨማሪም ህብረተሰቡ የራሱን መልዕክት ሲልክ 20 ብር ድጋፍ እንደሚያደርግም ነው የተገለፀው። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ያለውን ስሜት፣ሃሳብና መልዕክት ለታሪክ ከትቦ ማስቀመጥ የህዝባዊ ተሳትፎ አካል በመሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ መልዕክቱን በመግለፅ ለትውልድ የሚያስተላልፍበት ፕሮጀክት ማስፈለጉ ተገልጿል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ዩኒቨርሲቲው በአራት የትምህርት መርሃ ግብሮች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘ
Sep 2, 2025 27
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 27/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአራት የትምህርት መርሃ ግብሮች ዓለም አቀፍ እውቅና ማግኘቱን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ደረጀ እንግዳ (ዶ/ር) ገለጹ። ዶክተር ደረጀ እንግዳ እውቅናውን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና የሚሰጣቸው የትምህርት መርሃ ግብሮች ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲው አሜሪካ ከሚገኘው ዓለም አቀፍ የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ እውቅና ሰጭ ቦርድ /ABET/ በአራት የትምህርት መርሃ ግብሮች እውቅና ማግኘቱን አስታውቀዋል። እውቅናውን ያገኘው በመጀመሪያ ዲግሪ በሚሰጣቸው የባዮ-ቴክኖሎጂ፣ የምግብ ሳይንስ እና ሥነ ምግብ፣ የኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ እና የጂኦሎጂ የትምህርት መርሃ ግብሮች መሆኑን ጠቅሰዋል። እውቅናው ለተመራቂ ተማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ የሥራ ዕድሎችን እንደሚከፍት እና የትምህርት መረጃቸው ዓለም አቀፍ እውቅና እንዲኖረው የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ከመላው ዓለም ተማሪዎችን ተቀብሎ እንዲያስተምር ያስችለዋል ብለዋል።  
የጤና አገልግሎት ስርዓቱን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል ሥርዓት እንዲመራ የሚያስችል ተግባር እየተከናወነ ነው
Sep 1, 2025 164
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፡-የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የጤና አገልግሎት ስርዓቱን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል ሥርዓት እንዲመራ የሚያስችል ተግባር እያከናወነ መሆኑን ገለጸ። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ በባዮ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቱዩት እና በአፍሪካ ሲዲሲ ትብብር አለም አቀፍ የ "አሚክስ" ቴክኖሎጅ (AMICS) ኮንፈረንስ ዛሬ ተካሒዷል። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ የቴክኖሎጂ አማካሪ ስሜነው ቀስቅስ (ዶ/ር) በወቅቱ፤ "አሚክስ" (AMICS) ማለት የሴሎችና የፕሮቲኖች ቅንጣቶች ናቸው ብለዋል፡፡ የ"አሜክስ" ቴክኖሎጂ ማለት ደግሞ እነዚህን የሴሎችንና የፕሮቲኖች ቅንጣቶችን ለመመርመር የሚረዳ መሳሪያ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ መንግስት ባለፉት ዓመታት ቴክኖሎጂን ማዕከል ያደረጉ በርካታ ስራዎችን በመስራቱ በሁለንተናዊ ዘርፎች አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ዕለትም በተለይ የጤናው አገልግሎት ዘርፉን ከፍ ወዳለ ምዕራፍ በሚያሸጋግር በ"አሜክስ" ቴክኖሎጂ ጉዳይ ላይ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል። አሜክስ ቴክኖሎጂ የህክምና አይነት ሲሆን የዘረመል ምርመራዎችን ጨምሮ ክትባቶችንና ሌሎች መድሃኒቶችን በአገር ውስጥ እንዲካሔዱና እንዲመረቱ የሚያስችል ነው ብለዋል። ሰዎች በሚታመሙበት ወቅት የሰውነት ንጥረ ነገሮቻቸውን መርምሮ ትክክለኛ መድሃኒት በትክክለኛ ወቅት ለማሰጠት እንደሚያግዝም እንዲሁ፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ ከገባ የጤናውን ዘርፍ አገልግሎት እንደሚያልቀው ጠቁመው፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ቴክኖሎጂው እንዲገባ ከአለም አቀፍ ተመራማሪዎች ጋር በትብብር እንደሚሰራ ነው የተናገሩት። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄይሉ ኡመር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኮንፈረንሱ ዋና አላማ ዜጎች አለም የደረሰበትን የህክምና ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ "የአሚክስ" ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር በእውቀት ሽግግርም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ላይ የድርሻውን ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ በአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ በባዮ ኬሚስትሪ ዲፓርትመንት የባዮ ኬሚስትሪ ተባባሪ ፕሮፌሰር ሰለሞን ተበጅ በበኩላቸው፤ የአሚክስ ቴክኖሎጂው የጤና አገልግሎት ስርዓቱን የሚያልቅ ነው ብለዋል፡፡ ቴክኖሎጂው አካባቢን ቀድሞ በማወቅ ክትባቶችን ለማዘጋጅትና መዳህኒቶችን ለማምረት እንደሚረዳ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ተሞክሮ የሚወሰድባቸው መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ በጃፓን ሆካዶ የኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር ሲዳባሳቭ ጎወአ ናቸው፡፡  
የበካይ ጋዝ ልቀት መቀነሻ ቴክኖሎጂ ምቹና ጤናማ አካባቢ ለመፍጠር ያስችላል
Aug 30, 2025 268
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 24/2017(ኢዜአ)፦በካይ ጋዝ ልቀት መቀነሻ ቴክኖሎጂ በተሽከርካሪዎች ላይ መገጠሙ ምቹና ጤናማ አካባቢ ለመፍጠር እንደሚያስችል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ከተሽከርካሪ የሚወጣ በካይ ጋዝ ልቀት ቁጥጥር መመሪያ ከ2018 ዓ.ም መስከረም ጀምሮ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡ የበካይ ጋዝ ልቀት መመሪያ ቁጥር 1051/2017 ተግባራዊ ሲሆን፤ የአየር ብክለትን ከመቀነስ እና የነዳጅ አጠቃቀምን ከማሻሻል ባሻገር በተሽከርካሪዎች የቴክኒክ ጉድለት ሳቢያ የሚደርሰውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ ያግዛል።   መመሪያው ተሽከርካሪዎች የጋዝ ልቀታቸውን የሚቀንስ ቴክኖሎጂ በመግጠም የአየር ብክለት እንዲቀንስ የማድረግ ዓላማ ይዟል። የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሀሰን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከተሽከርካሪ የሚወጣን የካርቦን ልቀት ለመቀነስ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ትገኛለች። ከእነዚህ መካከል የነዳጅ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ በማገድ በምትካቸው የአየር ብክለት የማያስከትሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ የተሰራውን ስራ ለአብነት አንስተዋል፡፡   መመሪያው የበካይ ጋዝ ልቀት መጠን ደረጃን ያላሟሉ ተሽከርካሪዎች ልቀቱን ለመቀነስ የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን የመጠቀም ግዴታን የሚያስቀምጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ታልሞ የተዘጋጀው መመሪያው ከ2018 ዓ.ም መስከረም ጀምሮ በመላ አገሪቷ በሚገኙ ተሽከርካሪዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ ተሽከርካሪዎች የተቀመጠውን ደረጃ ካላሟሉ የበካይ ጋዝ ልቀት መቀነሻ ቴክኖሎጂውን መግጠም እንደሚጠበቅባቸው አስታውቀው፤ የጭስ ልቀትንና የነዳጅ አጠቃቀምን የሚያስተካክሉ ቴክኖሎጂዎች በበቂ ሁኔታ እየተዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መመሪያው ከተሽከርካሪዎች የሚወጣው የበካይ ጋዝ ልቀት በጤና ላይ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ እና ወደ ከባቢ አየር የሚለቀቀውን የሙቀት አማቂና በካይ ጋዝ ልቀት መጠንን ለመቀነስ የሚያስችል መሆኑ ተመልክቷል፡፡
የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ሳይንስና ቴክኖሎጂን በተሻለ መንገድ ለመረዳት አስችሎናል - ታዳጊዎች
Aug 28, 2025 394
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ሳይንስና ቴክኖሎጂን በተሻለ መንገድ ለመረዳት የሚያስችል ግንዛቤን ያስጨበጣቸው መሆኑን ታዳጊዎች ገለፁ። አምስት የዐውደ ርዕይ ምድቦችን የያዘው የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በይፋ መከፈቱ ይታወሳል። ቋሚ ኤግዚቢሽኑ በአርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የኢትዮጵያ ምላሽ፣ ግብርና ቴክኖሎጂ፣ የውኃ ኃይል እና ኢነርጂ፣ ኤሮኖቲክስ እና አቪየሽን ላይ ያተኮሩ የዐውደ ርዕይ ምድቦች ይዟል።   ኤግዚቢሽኑን ሲጎበኙ ኢዜአ ያነጋገራቸው ታዳጊዎች ጉብኝቱ የሰው ሰራሽ አስተውህሎትና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን በተሻለ መንገድ ለመገንዘብ እንደሚረዳ አብራርተዋል።   ቋሚ ኢግዚቢሽኑን ሲጎበኝ ያገኘነው ህፃን ሞገስ ሚልኪያስ በኤግዚቢሽኑ ሮቦትና ሌሎች የሰው ሰራሽ አስተውሎትና የተለያዩ ዘርፎች ቴክኖሎጂዎችን መመልከቱን ተናግሯል።   በእረፍት ጊዜው ኤግዚቢሽኑን መጎብኘቱ በትምህርት ቤት የተማራቸውን ነገሮች በተሻለ መንገድ እንዲረዳ እንዳስቻለው ገልጿል። ከአሜሪካ እንደመጣ የተናገረው ባርክኤል ዳዊት በበኩሉ በቋሚ ኤግዚቢሽኑ የተመለከታቸው ቴክኖሎጂዎች እንዳስደነቁት ነግሮናል።   ቋሚ ኤግዚቢሽኑ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለን እውቀት ለማጎልበት የሚረዳ ነውም ብሏል። ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ኢትዮጵያ በላቀ እድገት ላይ መሆኗን እንድገነዘብ አድርጎኛል ያለችው ደግሞ ሌላዋ ከአሜሪካ የመጣችው ኬብሮን ዳዊት ናት።   ከሃዋሳ የመጣው ሶፎንያስ ተስፋዬ በበኩሉ ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ስለ ሰው ሰራሽ አስተውህሎትና የአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም ውሃና ኢነርጂ ያለውን ግንዛቤ ለማሳደግ እንደረዳው ይናገራል።   ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ትውልዱን ለፈጠራ የሚያነሳሳና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን ለመወሰን የሚረዳ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ዳዊት ዓለሙ ናቸው። አስተያየት ሰጪዎቹ ተማሪዎች በተለይ በቀሪ የእረፍት ጊዜያቸው ኤግዚቢሽኑን በመጎብኘት የተሻለ የሳይንስና ቴክኖሎጂ እውቀት እንዲጨብጡም መልዕክት አስተላልፈዋል።   የአንድነት ፖርኮች ኮርፖሬሽን የህዝብ ግንኙነትና የኮሙዩኒኬሽን ባለሙያ ጌታቸው በየነ በበኩላቸው፤ የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን አሁን ላይ ያለውንና የወደፊቱን የቴክኖሎጂ ሁኔታ የሚያሳይ ነው ብለዋል።   ሳይንስ ለአገር ግንባታ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው፤ ኤግዚቢሽኑ ትውልዱ ሳይንስና ቴክኖሎጂን ተገንዝቦ የፈጠራ ክህሎቱን እንዲያዳብር የሚረዳ መሆኑን ተናግረዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ራሱን ከዳኝነት አገለለ
Sep 1, 2025 177
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 26/2017 (ኢዜአ)፦ ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ራሱን ከዳኝነት ዓለም ለማግለል መወሰኑን አስታውቋል። ያለፉትን ረጅም ዓመታት በወጥነት በሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መድረኮች በዳኝነት ያገለገለው ባምላክ ተሰማ ከዳኝነት ዓለም ራሱን ለማግለል መወሰኑን ለዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) በላከው መልዕክት ማሳወቁን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አመልክቷል። በዓለም ዋንጫ፣ የአፍሪካ ዋንጫ፣ በከፍሪካ አገራት ሻምፒዮና (ቻን) ፣ ካፍ ቻምፒየንስ ሊግ፣ ኮንፌሬዴሽን ዋንጫ፣ የዓለም ክለቦች ዋንጫ እና ኦሊምፒክን ጨምሮ በርካታ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ታላላቅ ጨዋታዎችን በመምራት የሀገሩን ስም ከፍ አድርጎ አስጠርቷል። ባምላክ ኢትዮጵያን በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ መድረክ በማገልገሉ ኩራት እንደሚሰማው ገልጾ ፊፋ ለሰጠው ዕድል በማመስገን ከኢንተርናሽናል ዳኝነት ራሱን ማግለሉን አስታውቋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባምላክ ተሰማ በዳኝነት ዓለም ላሳለፈው ህይወት እና አበርክቶ ያለውን አድናቆት እና ምስጋናውን አቅርቧል። በዳኝነት ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ ያበረከተው አስተዋፅኦ ሁሌም በኩራት የሚዘከር መሆኑን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ባምላክ በቀጣይ የህይወት ምዕራፉ መልካሙ ሁሉ እንዲገጥመውም ተመኝቷል። የ45 ዓመቱ ባምላክ ተሰማ ከእ.አ.አ 2009 አንስቶ በፊፋ የኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ሆኖ አገልግሏል። ባምላክ ተሰማ ከእግር ኳስ ዳኝነት በተጨማሪ የነርሲንግ ሙያ ተመራቂ ሲሆን በሕክምና ሙያ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኝ የጤና ተቋም ውስጥ በሙያው አገልግሏል። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሾሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ባምላክ ተሰማ ገና በልጅነቱ በስነ ፈለክ(አስትሮኖሚ) እውቀቱና ሳይንሳዊ ትንታኔው ብዙዎችን ያስገረመው የሮቤል ባምላክ አባት ነው።
በተጠባቂው ጨዋታ ሊቨርፑል አርሰናልን አሸነፈ
Aug 31, 2025 196
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2017(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሃ ግብር ሊቨርፑል አርሰናልን 1 ለ ዐ አሸንፏል። ማምሻውን በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የአማካይ ተጫዋቹ ዶምኒክ ስቦዝላይ በ83ኛው ደቂቃ ላይ ከረጅም ርቀት በግሩም ሁኔታ ያስቆጠረው ቅጣት ምት ለቀያዮቹ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አስገኝታለች። ሊቨርፑል በጨዋታው የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ቢወስድም የአርሰናልን ጠንካራ የተከላካይ መስመር ሰብሮ ለመግባት ሲቸገር ታይቷል። አርሰናል በቆመ ኳስ እና በክንፍ ከሚሻገሩ ኳሶች ግብ ለማስቆጠር ያደረገው ጥረት ፍሬያማ አልነበረም። የአርሰናል ተከላካይ ዊሊያም ሳሊባ በጨዋታው መጀመሪያ አካባቢ ባጋጠመው ጉዳት ተቀይሮ ገብቷል። ውጤቱን ተከትሎ የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ሊቨርፑል በዘጠኝ ነጥብ የሊጉን መሪነት ከቼልሲ ተረክቧል። በሊጉ የመጀመሪያ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርሰናል በስድስት ነጥብ ወደ ሶስተኛ ደረጃ ዝቅ ብሏል። ቀደም ብለው ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች፤ ብራይተን ማንቼስተር ሲቲን 2 ለ 1 እንዲሁም ዌስትሃም ኖቲንግሃም ፎረስትን 3 ለ 0 አሸንፈዋል። የዛሬው የጨዋታ መርሐ ግብር ሲቀጥል፤ ምሽት 3 ሠዓት ላይ አስቶንቪላ ከክሪስታል ፓላስ ይገናኛሉ።
ብራይተን ማንቼስተር ሲቲን አሸንፏል
Aug 31, 2025 156
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2017 (ኢዜአ)፡- በሦስተኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በሜዳው ማንቼስተር ሲቲን ያስተናገደው ብራይተን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ሃላንድ የውኃ ሰማያዊዮቹን መሪ ያደረገች ግብ በ34ኛው ደቂቃ አስቆጥሮ ወደ መልበሻ ክፍል ማምራት ችለው ነበር። ሆኖም ከእረፍት መልስ ሚልነር በ67ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ብራይተንን አቻ ማድረግ የቻለች ግብ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል። እንዲሁም ግሩዳ በ89ኛው ደቂቃ የማሸነፊያዋን ግብ አስቆጥሮ፤ ብራይተን ሦስት ነጥብ ማሳካት ችሏል።   በሌላ የዛሬ መርሐ ግብር ዌስትሃምን ያስተናገደው ኖቲንግሃም ፎረስት 3 ለ 0 ተረትቷል። የዌስተሃምን ግቦችም ቦውን በ84ኛው፣ ፓኩዌታ በፍጹም ቅጣት ምት በ88ኛው እንዲሁም ዊልሰን በ91ኛው ደቂቃ ማስቆጠር ችለዋል። ቀሪ የዛሬ መርሐ ግብሮች መካሄዳቸውን ሲቀጥሉ፤ አመሻሽ 12 ከ30 የሣምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ በሊቨርፑልና አርሰናል መካከል ይደረጋል። እንዲሁም ምሽት 3 ሠዓት ላይ አስቶንቪላ ከክሪስታል ፓላስ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ተጀምሯል
Aug 31, 2025 170
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2017(ኢዜአ)፦ የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በአበበ በቂላ ስታዲየም ተጀምሯል። በሊጉ የመክፈቻ ጨዋታ አዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል።   በአሁኑ ሰዓት አርባምንጭ ከተማ ከይርጋጨፌ ቡና ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። ሲዳማ ቡና ከቦሌ ክፍለ ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመጀመሪያ ሳምንት ከአዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ ሊያደርግ የነበረው ጨዋታ ቡድኑ በካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ተሳትፎው ምከንያት መራዘሙን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የንግድ ባንክ የሊጉ የመጀመሪያ ሶስት ጨዋታዎች በተስተካካይ መርሃ ግብር እንደሚያዙም አመልክቷል። የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት እስከ ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል። የውድድሩ የመጀመሪያ ዙር መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ይካሄዳል። በሊጉ ላይ 14 ክለቦች ይሳተፋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
ቦረና ብሔራዊ ፓርክ ከ286 በላይ የአዕዋፍ ዝርያዎች መኖሪያ ሲሆን አራቱ በብቸኝነት ይገኙበታል
Aug 31, 2025 231
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2017 (ኢዜአ)፡- ከ1 ሺህ የሚልቁ የእጽዋት ዝርያዎች መገኛ የሆነው የቦረና ብሔራዊ ፓርክ አቀማመጡ (ተፈጥሮው) ድንቅ መሆኑን የፓርኩ ዋርድ ንጉሴ ዋታ ገልጸዋል። ከ286 በላይ አዕዋፋት እንደልብ የሚናኙበት መሆኑንና ከእነዚህ ውስጥ አራቱ በቦረና ብሔራዊ ፓርክ ብቻ የሚገኙ ናቸው ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል። በተጨማሪም ከ46 በላይ የአጥቢ እንስሣት እና ከ1 ሺህ በላይ የእጽዋት ዝርያዎች መኖሪያ ነው ይላሉ። በፓርኩ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር በቋሚ እና ጊዜያዊ በማኅበር በማደራጀት ጭምር በተለያዩ ዘርፎች ለበርካታ ወገኖች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉንም አንስተዋል። ይህን ለበርካቶች የገቢ ምንጭ የሆነ ፓርክ ሕብረተሰቡ እና መንግሥት በትኩረት እየጠበቁት መሆኑን እና አበረታች ውጤት መገኘቱን ይገልጻሉ። ለጎብኚዎች ምቹ መሆኑን ጠቁመው፤ ከያቤሎ በአራቱም አቅጣጫዎች የቦረና ብሔራዊ ፓርክን ማግኘት እንደሚቻል ጠቅሰዋል። አሁን ላይ አጠቃላይ ስፋቱ 6 ሺህ 700 ኪሎ ሜትር ስኩየር መሆኑን አንስተው፤ ቀደም ሲል የእንስሳት መጠለያ እንደነበርና ከሰኔ 2005 ዓ.ም ጀምሮ በተደራጀ አግባብ ብሔራዊ ፓርክ ሆኗል ይላሉ። በአቀማመጡ ለዕይታ ከመማረክ በተጨማሪ ለአዕዋፋት፣ የተለያዩ የዱር እንስሣት እና በርካታ እጽዋት ዓይነቶች መገኛ የሆነውን ፓርክ በዩኔስኮ ለማስመዝገብ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል። ፓርኩ ሰላማዊ፣ ጽዱ እና ለነዋሪዎች ምቹ መሆኑን ገልጸው፤ ወደ ፓርኩ ለሚመጡ ጎብኚዎች የመጓጓዣ አማራጭ ከመስፋቱ ጋር በተያያዘ በቀጣይ የማረፊያ ሆቴል እና ሎጂ በሥፋት መሠራት እንደሚኖርበት አመላክተዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ያቤሎ አውሮፕላን ማረፊያ በሳምንት ሦስት በረራዎችን ለማድረግ የሚያስችለውን ዝግጅት ማጠናቀቁን ማሳወቁ ይታወሳል። የአየር ትራንስፖርት መጀመሩ የጎብኚዎችን የመጓጓዣ አማራጭ በማስፋት የጎብኚዎች ቁጥር እና በዚያው ልክ የፓርኩና የአካባቢው ማኅበረሰብ ተጠቃሚነት እንደሚያድግ አቶ ንጉሴ ተናግረዋል።
ሁለተኛው ዓለም አቀፍ አየር ንብረት ለውጥ ሳምንት በቀጣዩ ሳምንት በኢትዮጵያ ይካሄዳል
Aug 31, 2025 188
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2017(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ያዘጋጀው ሁለተኛው ዓለም አቀፍ አየር ንብረት ለውጥ ሳምንት ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜን 1 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ እንደሚደረግ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ። ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፤ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" መሪ ሀሳብ ይካሄዳል። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት እና ከግሎባል ግሪን ግሮውዝ ኢኒስቲትዩት ጋር በመሆን የጉባኤውን ዝግጅት በማስመልከት ለጋዜጠኞች ያዘጋጀው የግንዛቤ መፍጠሪያ ስልጠና ትናንት በቢሾፍቱ ከተማ ተካሄዷል።   ከጉባኤው አስቀድሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ማዕቀፋዊ ስምምነት (UNFCC) ያዘጋጀው ሁለተኛው ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ሳምንት ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜን 1 2017 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል። ሳምንቱ “ውይይቶችን ወደ ተግባር እና ውጤት መቀየር” በሚል ዋና ሀሳብ የሚከናወን ሲሆን የአየር ንብረት ለውጥ ቃል ኪዳኖችን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ውጤት መቀየር ላይ ያተኮረ ነው። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነትና ስትራቴጂክ አጋርነት መሪ ስራ አስፈፃሚ መንሱር ደሴ በአየር ንብረት ለውጥ ሳምንቱ 1 ሺህ 500 ገደማ ልዑክ እንደሚሳተፍ ገልጸዋል። በሳምንቱ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ችግኝ ዋንኛ ሰለባ ናቸው ከሚለው የቆየ ትርክት በመውጣት አህጉሪቷ ለጉዳዩ መፍትሄ አፍላቂ የሆኑ የተግባር ምላሾችን እየሰጠች መሆኑ የሚታይበት ነው ብለዋል።   አፍሪካ ከቃል ኪዳኖች ባለፈ ለአየር ንብረት ለውጥ ዘላቂ መፍትሄ እንዲበጅት ሀገር በቀል መፍትሄዎችን እየተገበረች መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ አማካኝነት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ ማንንም ሳትጠብቅ ተጨባጭ እርምጃ መውሰዷን ተናግረዋል። አረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ ለምግብ ዋስትና መረጋገጥና ለሀገር እድገት የበኩሉን ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ነው መሪ ስራ አስፈጻሚው ያብራሩት። ኢትዮጵያ ግብርናውን ጨምሮ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ የታገዙ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል እርምጃዎች እየሰወደች እንደምትገኝ አመልክተዋል። የአየር ንብረት ሳምንቱ የሀገራት ትልሞች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቶች ወደ ተጨበጠ ለውጥ እንዲቀየር ጠንካራ ጥሪ የሚቀርብበት ነው ብለዋል። ሳምንቱ ለሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ የሚሆኑ የፖሊሲ ሀሳቦችን የሚመመግብና በብራዚል ቤለም ለሚካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ 30) የጋራ አጀንዳን ለመቅረጽ እንደሚያግዝ አክለዋል። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በአየር ንብረት አጀንዳ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያላቸውን ሁነቶች የኢትዮጵያ እና የአፍሪካን ጥቅምና ፍላጎት በማጎላት መዘገብ እንደሚኖርባቸው አቶ መንሱር አስገንዝበዋል። በሁለተኛው የአየር ንብረት ሳምንት የአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ አመራሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ወጣቶች፣ የቴክኒክ ባለሙያዎች እና ሌሎች የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በሳምንቱ የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች፣ የጎንዮሽ ውይይቶች፣ የልምድ ልውውጦች፣ አውደ ርዕዮች እና የትስስር ማጠናከሪያ መድረኮች ይከናወናሉ። ሳምንቱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በዓመት ሁለት ጊዜ የሚያካሂደው የአየር ንብረት ለውጥ ሳምንት ሁነቶች አካል ነው። የእ.አ.አ የ2025 የመጀመሪያ የአየር ንብረት ሳምንት (CW1) እ.አ.አ በሜይ ወር 2025 በፓናማ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የሳምንቱ ሁነት አላማ የአየር ንብረት ለውጥ ቃል ኪዳኖች ወደ ተግባር እንዲለወጡ ንቅናቄ ለመፍጠር እና ቀጣይ ለሚደረጉ ሁነቶች አጀንዳ መቅረጫ መድረክ ሆኖ ማገልገል መሆኑን ተመድ አስታውቋል።
ኢትዮጵያ በጉባኤው ላይ የአፍሪካን የአየር ንብረት ለውጥ የፋይናንስ ተደራሽነት አጀንዳን በስፋት ታንጸባርቃለች
Aug 30, 2025 218
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 24/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በሁለተኛው የአፍሪካ ንብረት ጉባኤ ላይ የአፍሪካን የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ የማግኘት አጀንዳን አጉልታ እንደምታሰማ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን ገለጹ። ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ጉባኤው የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ህብረት በጋራ ያዘጋጁት ነው። ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፤ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። በጉባኤው ላይ ከ20 ሺህ እስከ 25 ሺህ ልዑካን ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት እና ከግሎባል ግሪን ግሮውዝ ኢኒስቲትዩት ጋር በመሆን የጉባኤውን ዝግጅት በማስመልከት ለጋዜጠኞች ያዘጋጀው የግንዛቤ መፍጠሪያ ስልጠና በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን፥ ኢትዮጵያ በቅርቡ ሁለት ትላልቅ ሁነቶችን እንደምስታናግድ ገልጸዋል። ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ እና የአፍሪካ አየር ንብረት ሳምንት እንደሚከናወን አመልክተዋል። የአየር ንብረት ሳምንቱ ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ተናግረዋል። ጉባኤው የአፍሪካን የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎች እና የተግባር ምላሾች ጎልተው የሚታዩበት እንደሆነ ተናግረዋል። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ገፈት ቀማሽና የገንዘብ ጠያቂ ብቻ ሳይሆን የመፍትሔ ምንጭ የሆነች አህጉር መሆኗን የሚታይበት እንደሆነ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በጉባኤው በአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ ያላትን የመሪነት ሚና በመወጣት የትርክት ለውጥ እንዲመጣ ትሰራለች ብለዋል። በካይ ሀገራት የገቡትን የፋይናንስ ቃል ኪዳን ተፈጻሚነት ጉዳይ ላይ ድምጿን በማሰማት የአፍሪካን የፍትሐዊነት ጥያቄ እንደምታቀርብ ነው የተናገሩት። ከጉባኤው በኋላ የአየር ንብረት ለውጥን የተመለከተ የአዲስ አበባ ድንጋጌ ይፋ እንደሚደረግና ለተፈጻሚነቱ በትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል። እስከ አሁን ባለው መረጃ መሪዎችን ሳይጨምር 21 ሺህ 600 በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ መመዝገባቸውን ነው የጠቆሙት። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉ አመልክተዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያ በቀጣይ ሌሎች ዓለም አቀፍ ሁነቶችን ለማስተናገድ መሰረት እንደሚጥል ተናግረዋል። ጋዜጠኞች በሁነቶቹ ላይ የተሟላ ግንዛቤ እንዲኖራቸው በማድረግ ውጤታማ ዘገባ እንዲሰሩ ለማድረግ ስልጠናው መዘጋጀቱን ነው የገለጹት። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የአፍሪካ መልካም ገጽታን እና የአፍሪካን የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎች ማጉላት እንዳለባቸው አሳስበዋል። መሪዎች የገቧቸው የአየር ንብረት ለውጥ ቃልኪዳኖች ትግበራ ተጠያቂነት እና የአዲስ አበባ ድንጋጌ ተፈጻሚነትና አተገባበር ላይ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የአየር ንብረት የሳይንስ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰው፣ የልማት እና የህልውና ጉዳይ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፥ በዚህ ረገድም ጋዜጠኞች ጉዳዩን በውል ተረድተው ለማህበረሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራን እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርበዋል። በስልጠናው ላይ ሁለተኛውን የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ እና የአፍሪካ የአየር ንብረት ሳምንት ዝግጅት አስመልክቶ የተዘጋጁ ጽሁፎች ቀርበው ውይይቶች ተደርገዋል። በጉባኤው ላይ በኢትዮጵያና አፍሪካ ህብረት የጋራ ጥምረት 51 ሁነቶች የሚካሄዱ ሲሆን የልማት አጋሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ያዘጋጇቸው 186 ሁነቶች ተዘጋጅተዋል። 24 መካነ ርዕዮች (ፓቪሊዮኖች) ተዘጋጅተው የአፍሪካን የአየር ንብረት ለውጥ መካከል ስራዎች አውደ ርዕዮች ይካሄዳሉ።
የአረንጓዴ ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ስራ የ"አረቅጥ " ሀይቅን ከጉዳት በመታደግ ለቱሪዝም ዘርፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Aug 30, 2025 218
ወልቂጤ ፤ነሐሴ 24/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ሲከናወን የቆየው የአረንጓዴ ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ስራ የ "አረቅጥ" ሀይቅን ከጉዳት በመታደግ ለቱሪዝም ዘርፉ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ ተገለጸ። ‎የ"አረቅጥ" ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ሰብስቤ ተካ እንዳመለከቱት፤ በከተማው አቅራቢያ የሚገኘው የ"አረቅጥ" ሀይቅ በዙሪያው ባጋጠመው የአፈር መሸርሸርና የደለል ጉዳት ሊደርቅ ተቃርቦ ነበር። ሀይቁን ለመታደግም በተፋሰስ የማልማትና ወደ ሀይቁ የሚገባውን ደለል የመከላከል ስራ ተሰርቷል ብለዋል። በተለይም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ከማልማት ባለፈ በአቅራቢያው የነበሩ ባህር ዛፍን ጨምሮ ሌሎችም ውሃ የመምጠጥ እና የመሬት ለምነት የሚያሳጡ ተክሎች የማንሳትና የእርከን ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ነው ያወሱት።   በዚህም በአጠቃላይ ከ25 ሄክታር በላይ የሚሸፍን በሀይቁ ዙሪያ ተጎድተው የነበሩ አካባቢዎች እንዲያገግሙ መደረጉን ተናግረዋል። ይህንን ተከትሎም ሀይቁ መልሶ ማገገሙን አንስተው፤ በአረንጓዴ አሻራ ልማት ተፈጥሮን መመለስና ውብ አካባቢ ማድረግ እንደሚቻል ተጨባጭ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።   በተጨማሪም ሀይቁ ለ"አረቅጥ " ከተማ ተጨማሪ ውበት ወደመሆን መድረሱን ያነሱት አቶ ሰብስቤ፤ ለቱሪዝም ዘርፉ ምቹ አካባቢ በመሆን በርካቶች የሚዝናኑበትና የስራ ዕድል መፍጠሪያ መሆን መቻሉን አስረድተዋል። 5 ማህበራት በዓሳ ማስገር እና በመዝናኛ ጀልባ አቅርቦት መሰማራታቸውን እና ለበርካቶች የስራ ዕድል ማስገኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ በሀይቁ የዓሳ ምርትና የመዝናኛ አገልግሎት የማስፋት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።   ‎በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የዓሣ ሀብት ተመራማሪ ይርጋ እናውጋው (ዶ/ር) ፤ አካባቢን በአግባቡ ማልማትና ተፈጥሮን መጠበቅ የውሃ አቅምን ለመጨመር ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአካባቢው በተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ወደ ቀድሞ ተፈጥሯዊ ይዘቱ እየተመለሰ ያለው የ"አረቅጥ" ሀይቅ የተለያዩ የዓሳ ዝርያዎችና መጠን እየጨመረ መሆኑን ጠቅሰዋል ። ‎ሀይቁን ለኢኮ ቱሪዝም ልማት በማዋል ገቢ ማመንጨትና ተጨማሪ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ምቹ መደረጉን ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በአህጉራዊ ትስስር ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Aug 26, 2025 485
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በአህጉራዊ ትስስር አጀንዳ ያላቸውን ትብብር የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰሩ አስታወቁ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት(ጄኔቫ) የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኛ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሴኤ) ዋና ፀሐፊ ክላቫር ጋቴቴ ጋር ተወያይተዋል።   ሁለቱ ወገኖች አፍሪካ በዓለም መድረክ አንድ የጋራ ድምጽ እንዲኖራት ማድረግ ያለውን ወሳኝ ጠቃሜታ አጽንኦት ሰጥተው መክረውበታል። የአፍሪካ ህብረት እና ኢሲኤ በንግድ፣ቀጣናዊ ትስስር እና የአፍሪካ የአዕምራዊ ንብረትን የበለጠ አጀንዳ ማራመድ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።   ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት(ጄኔቫ) የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው በሐምሌ ወር 2017 ዓ.ም መሾማቸው የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ህብረት እና ኢሲኤ ትብብራቸውን እ.አ.አ በ1960ዎቹ መግቢያ ላይ መጀመራቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ።
አፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት በትብብር ይሰራሉ
Aug 24, 2025 447
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 18 /2017 (ኢዜአ)፦አፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት በትብብር እንደሚሰሩ አስታወቁ። ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም(ቲካድ) በዮካሃማ መካሄዱን ቀጥሏል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከፎረሙ ጎን ለጎን ከጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ፕሬዝዳንት አኪሂኮ ታናካ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።   የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የጃይካ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንዲሁም ኢኮኖሚና ማህበራዊን ጨምሮ በአፍሪካ ቁልፍ ዘርፎች እያደረገ ያለውን ኢንቨስትመንት አድንቀዋል። ሊቀ መንበሩ እና ፕሬዝዳንቱ የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ያላቸውን የጋራ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ዘጠነኛውን የቲካድ ፎረም መንፈስ ወደ ዘላቂ የኢኮኖሚ ለውጥ በጋራ የመፍጠር ምዕራፍ ማሸጋገር እንደሚገባም አንስተዋል። ከነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው ፎረም የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ፤ የአህጉር በቀል መፍትሄዎች መድረክ 
Aug 23, 2025 450
በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን የአየር ንብረት በርቀት የሚያዩት ስጋት ሳይሆን የዕለት ተዕለት እውነታቸው ነው። በጎርፍ ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች እና ተጠራርገው የሚወሰዱ ንብረቶች፣ በተከታታይ ድርቆች ምክንያት የሚያጋጥመው የምርታማነት መቀነስ የአየር ንብረት ለውጥ ከወለዳቸው ቀውሶች መካከል ይጠቀሳሉ። እነዚህ በተጨባጭ የዜጎችን ኑሮ እየተፈታተኑ ያሉ ችግሮች በአፍሪካ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ስነ ምህዳር ላይ ለውጥ እንዲመጣ አስገድደዋል። የድህነት ምጣኔ እና የተፈናቃይ ዜጎች እየጨመረ መምጣት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽእኖዎችን በተግባር የገለጡ ጉዳዮች ሆነዋል።   አፍሪካ ለዓለም የበካይ ጋዝ ልቀት ከአራት በመቶ በታች ድርሻ ቢኖራትም የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳት ከፍተኛ ቀንበር የሚያርፍባት አህጉር ሆናለች። ከሳህል ቀጣና የበረሃማነት መስፋፋት እስከ ምስራቅ አፍሪካ ኃይለኛ ጎርፎች የአህጉሪቷ ዜጎች በጣም ውስን ድርሻ ባላቸው ጉዳይ የቀውሱ ከፍተኛ ሰላባ እየሆኑ ነው። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የአስቸኳይ ጊዜ ውስጥ ናት ቢባል ማጋነን አይሆንም። እንደ ዓለም አቀፉ የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት መረጃ ከእ.አ.አ 1991 እስከ 2022 ባለው ሶስት አስርት ዓመታት ባሉ እያንዳዱ አስርት ዓመታት በአፍሪካ በአማካይ የ0 ነጥብ 3 ዲግሪ ሴልሺየስ የሙቀት ጭማሪ ተመዝግቧል። እ.አ.አ በ2024 የዓለም ሙቀት በ1 ነጥብ 2 ዲግሪ ሴልሺየስ ጨምሮ በዓለም ታሪክ ከፍተኛው ሙቀት የተመዘገበበት ዓመት ነበር። 2024 በአፍሪካ የሙቀት መጠን 0 ነጥብ 86 በመቶ በመጨመር በአህጉሪቷ ታሪክ ከፍተኛው ሙቀት የተዘመገበበት ዓመት ሆኖም ተመዝግቧል። ከሙቀቱ በአሳሳቢ ሁኔታ መጨመር ባሻገር ድርቅ፣ ጎርፍ እና የምግብ ዋስትና ስጋት ላይ መውደቅ ሌሎች የአፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች ናቸው። እ.አ.አ 2024 ደቡባዊ አፍሪካ ክፍል በቅርብ አስርት ዓመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ድርቅ አጋጥሟታል። በድርቁ ምክንያት ዛምቢያ እና ዚምባቡዌ የሰብል ምርታቸው በ50 በመቶ ቀንሷል። በምስራቅ እና ማዕከላዊ አፍሪካ በቅርብ ጊዜ የተከሰቱ ከባድ ጎርፎች ሚሊዮኖችን አፈናቅለዋል፤ የዜጎች ህይወት አመሰቃቅላዋል መሰረተ ልማቶችንም አውድመዋል። የዓለም አቀፉ ሜትሮሎጂ ድርጅት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካን ከሁለት እስከ አምስት በመቶ ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) ወጪ እየወሰደ ይገኛል። አንዳንድ ሀገራት ለአየር ንብረት አስቸኳይ ምላሽ ዘጠኝ በመቶ ጥቅል ሀገራዊ ምርታቸውን ፈሰስ ያደርጋሉ። አፍሪካ በየዓመቱ ከ30 እስከ 50 ቢሊዮን ዶላር ለአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ አቅዶች ትግበራ ቢያስፈልጋትም ከዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ ውስጥ የምታገኘው ገንዘብ ከአንድ በመቶ በታች ነው። የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት የ2024 የአፍሪካ ሪፖርት የአፍሪካ የግብርና ምርታማነት ከእ.አ.አ 1961 በኋላ በ34 በመቶ መቀነሱን ይገልጻል። የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ ሀገራት ምግብ ለመግዛት የሚያወጡት 35 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ወጪ እ.አ.አ በ2025 ማብቂያ ወደ 110 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ከፍ እንደሚል ገልጿል። የበረሃማነት መስፋፋት፣ የብዝሃ ህይወት መመናመን፣ የጤና እክሎች፣ መፈናቀል እና የታሪካዊ ቅርሶች አደጋ ላይ መውደቅ አፍሪካ እየገጠሟት ያሉ የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽእኖዎች ውጤት ናቸው። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት በየዓመቱ 250 ቢሊዮን ዶላር ቢያስፈልጋትም እያገኘች ያለችው 30 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ስጋት አፍሪካ የጥያቄ አምሮት ኖሮባት የምታነሳው አጀንዳ ሳይሆን የፍትህ እና የህልውናዋ ጉዳይም ጭምር ነው። በአዲስ አበባ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፥ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አህጉሪቷ እየገጠሟት ካሉ አንገብጋቢ ፈተናዎችን በዘላቂነት መሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይመክራል። የሀገራት መሪዎች፣ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ወጣቶች እና የግሉ ዘርፍ በአንድነት ይወያያሉ። በጉባኤው ላይ አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በታዳሽ ኢነርጂ፣ ዘላቂ ግብርና እና ተፈጥሮ ተኮር መፍትሄዎች ጨምሮ በአፍሪካ ያሉ አረንጓዴ የመፍትሄ ሀሳቦች የበለ ማላቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሀገራት ተሞክሯቸውን ያቀርባሉ። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ በየዓመቱ የሚያጋጥማትን የ220 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ አቅርቦት ክፍተት መሙላት እና አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም ላይ ምክክር ይደረጋል። በብራዚል ቤለም በሚካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ 30) ጨምሮ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ድርድሮች ላይ የአፍሪካን ፍላጎቶች እና ጥቅሞች ማስጠበቅ የሚያስችል የጋራ እና ጠንካራ አቋም መያዝ ከጉባኤው የሚጠበቅ ውጤት ነው። የአፍሪካ ሀገራት በጉባኤው ላይ የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል የሚያስችሉ ተጨባጭና መሬት ላይ የወረዱ እቅዶቻቸው ላይ የሚያቀርቡ ሲሆን የገቡትን ቃል ኪዳን ወደ ተግባር መቀየራቸውን የሚከታተል የቁጥጥር ስርዓት ትግባራትን የሚያጠናክሩባቸው መንገዶችን በማቅረብ በአጠቃላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ቃልኪዳናቸውን ዳግም ያድሳሉ።   አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ችግሮች ገፈት ቀማሽ ሳትሆን የመፍትሄዎች እና የአይበገሬነት ስራዎች ማሳያም ናት። የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ እና አከባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የኬንያ የእንፋሎት እና የፀሐይ ኃይል ኢንሼቲቮች እንዲሁም የሞሮኮ ኑር ኦውርዛዛቴ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አረንጓዴ ልማት ሊሆን የሚችል ብቻ ሳይሆን በተጨባጭ የሚሳካ መሆኑን አፍሪካ ማረጋገጫ እንደሆነች በግልጽ የሚያመላክት ነው። አፍሪካ ከዓለም ዋንኛ በካይ ጋዝ ለቃቂ ሀገራት ገንዘብ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን ሀገር በቀል የፋይናንስ እና ሀብት ማሰባሰብ አቅማቸውን የበለጠ ማሳደግ ይጠበቅባታል። የአዲስ አበባው ጉባኤም የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ አቅርቦታቸውን እንዲጨምሩ ጥሪ የሚቀርብበት ነው። አፍሪካውያን እንደ አረንጓዴ አሻራ ያሉ ከንግግር ያለፉ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን በመተግበር አይበገሬ አቅም ሊገነቡ ይገባል። የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ሀገር በቀል የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎችን ከዓለም አቀፍ አጋርነት ጋር ከማዛመድ አኳያ ያላው ሚና ወሳኝ የሚባል ነው። ጉባኤው አፍሪካ ከአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ትርክት ወደ መፍትሄ አፍላቂነት እና የግንባር ቀደም ሚና አበርካችነት ለመሸጋገር እንደ መስፈንጠሪያ የሚያገለግል ትልቅ እድል ነው። የአዲስ አበባው ጉባኤ ከስብስባ ባለፈ አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ቆርጣ ለተነሳችበት የተግባር ምላሽ ጉዞ እና የዓለም አቀፍ ተጠያቂነት መረጋገጥ የጋራ ትግል ውስጥ ትልቅ እጥፋት ሊሆን ይችላል።  
በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የአንድ ሀገር የመልማት እና የማደግ ፍላጎት ሊገደብ አይገባም - አንቶኒዮ ጉቴሬዝ
Aug 5, 2025 883
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2017(ኢዜአ)፦መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የአንድን ሀገር የመልማት እና የማደግ መብት በፍጹም መወሰን የለበትም ሲሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ። ሶስተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ኮንፍረንስ ዛሬ በተርኪሚኒስታን መካሄድ ጀምሯል።   በኮንፍረንሱ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ፣እስያ፣አውሮፓ እና ደቡብ አሜሪካ የሚገኙ 32 ሀገራት ተሳታፊ ሆነዋል። ከተሳታፊዎቹ ሀገራት መካከል 16 ከአፍሪካ ናቸው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ያሉባቸውን የልማት፣የኢኮኖሚ እና የእድገት ፈተናዎችን አንስተዋል። በማደግ ላይ የሚገኙ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት የመልማት አቅማቸው ባሉበት መልክዐ ምድራዊ ስፍራ ምክንያት ሊገደብ እንደማይገባ አመልክተዋል። ዋና ፀሐፊው የባህር በር የሌላቸው ሀገራት የዓለምን ሰባት በመቶ ህዝብ የያዙ ቢሆንም በዓለም ኢኮኖሚና ንግድ ውስጥ ያላቸው ድርሻ ከአንድ ፐርሰንት ጥቂት ሻገር ያለ መሆኑን ገልጸው ይህ ትልቅ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ሲሉ ተናግረዋል። በተጨማሪም ሀገራቱ ለአየር ንብረት ለውጥ ያላቸው ድርሻ ዝቅተኛ ቢሆንም የጉዳቱ ዋንኛ ሰለባ መሆናቸውን አንስተዋል። የዓለም ማህበረሰብ ሀገራቱ በዓለም ኢኮኖሚ እና የንግድ ስርዓት ውስጥ ያላቸው ድርሻ እንዲያድግ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።   የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የንግድ እሴት ሰንሰለት ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ እንዲጨምር የሚያስችል መዋቅራዊ ለውጥ ያሻል ያሉት ዋና ፀሐፊው፥ ይህም ሀገራት ጥሬ ምርቶችን ከመላክ ከፍተኛ እሴት ያለው ምርት ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ ያደርጋል ነው ያሉት። የባለብዙ ወገን የልማት ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት አነስተኛ ወለድ ያለው የፋይናንስ አቅርቦት ለሀገራት ተደራሽ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከትስስር ጋር በተያያዘ የሚገጥማቸውን የመሰረተ ልማት እና መዋቅራዊ ችግሮች መፍታት እንደሚገባ አመልክተዋል። ለዚህም ድንበር ተሻጋሪ አሰራሮችን ማቅለል፣የተለያዩ የመመዘኛ ደረጃዎችን ማጣጣም እንዲሁም የተሳለጠ ንግድና ትራንዚት እንዲኖር የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ነው ያነሱት። ጉቴሬዝ በመሰረተ ልማት መጠነ ሰፊ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ያሉ ሲሆን የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት የማይበገር የትራንስፖርት መተላለፊያ መስመር፣ ድንበር ተሻጋሪ የእርስ በእርስ የኢነርጂ ትስስር፣ ሰፊ የአየር ትስስር እና በቴክኖሎጂ የታገዙ የሎጅስቲክስ አውታሮች እንደሚያስፈልጋቸው አስገንዝበዋል። ሀገራቱ ያለባቸውን የመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ እክሎች ምላሽ ለመስጠት ፍትሃዊ የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትን ማስፈን እንዳለባቸው አሳስበዋል።   ኮንፈረንሱ ላይ ኢትዮጵያ እና የባህር በር የሌላቸው ሌሎች ሀገራት በዓለም የንግድ ስርዓት ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ በትስስር፣ በፍትሃዊ የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነት እና ዓለም አቀፍ ትብብር እንዲያድግ ግፊት እንደሚያደርጉ ተመላክቷል። ሶስተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ኮንፍረንስ እስከ ነሐሴ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
ሐተታዎች
ከ500 በላይ ሥራዎችን የሚያሳልጠው ጉበት … 
Sep 1, 2025 92
ጉበት ከ500 በላይ ሥራዎችን የሚያከናውን ዋነኛ እና ሁለገብ የሰውነታችን አካል ነው ይላሉ በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የጨጓራ፣ አንጀት እና ጉበት ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር አብዲ ባቲ። የጉበት ተግባራት በአራት ዐቢይ ክፍሎች እንደሚከፈሉም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። 👉 የመጀመሪያው ተግባሩ፤ ጎጂ ንጥረ ነገሮችን ከደም ውስጥ ማጽዳት፣ ቆሻሻ ምርቶችን ማስወገድ፣ የመድኃኒቶችን ሜታቦሊዝም ማከናወን፣ ከምንበላው፣ ከምንጠጣው እና ከምንተነፍሰው ሁሉ መርዞችን ማስወገድ ነው ይላሉ። 👉 እንዲሁም ሁለተኛው ተግባሩ፤ ቫይታሚኖችን፣ ማዕድናትን እና ኃይልን ማከማቸት መሆኑን ገልጸው፤ ለሰውነታችን ማበረታቻ ኃይል በሚያስፈልግበት ጊዜ ዝግጁ ማድረግ ነው ብለዋል። 👉 ሦስተኛው ተግባር ደግሞ፤ ለደም መርጋት እና ኢንፌክሽኖችን ለመዋጋት ፕሮቲኖችን ማመንጨት መሆኑን ያስረዳሉ። 👉 አራተኛው ተግባሩን ሲያብራሩም፤ ‘Bile’ የሚባል ንጥረ ነገር በማምረት ከሚወዷቸው (ከሚመገቧቸው) ምግቦች ውስጥ የሚገኘውን ስብ እንዲፈጭ ያደርጋል ሲሉ ገልጸዋል። ጉበትን ለህመም የሚያጋልጡ መንስኤዎች ምንድን ናቸው? • እንደ ዶክተር አብዲ ገለጻ፤ ጉበት ዘርፈ ብዙ ተግባራት ያለው ወሳኝ የሰውነት አካል እንደመሆኑ ለብዙ አደጋዎች ይጋለጣል። ከነዚህ አጋላጭ ምክንያቶች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ ናቸው ብለዋል። 👉 እንደ ሄፓታይተስ ቢ እና ሲ ባሉ ቫይረሶች በደም፣ በመርፌ ወይም ወሊድ ወቅት የሚተላለፉ፤ 👉 ከመጠን በላይ አልኮል መጠቀም፤ 👉 ከመጠን በላይ መወፈር ፤ 👉 የስኳር በሽታ፤ 👉 ከእፅዋት እና የተለያዩ እህሎች (ለምሳሌ ከማሽላ እና በቆሎ) ውስጥ የሚገኙ እንደ አፍላቶክሲን ያሉ መርዛማ ንጥረ ነገሮች ይገኙበታል ብለዋል። 👉 በተጨማሪም ከ40 ዓመት በላይ መሆን፣ በቤተሰብ የሚተላለፉ የጉበት በሽታዎች መኖር፣ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እና አደገኛ ልማዶች ለጉበት በሽታ ከሚያጋልጡ መንስዔዎች መካከል ናቸው ይላሉ። ከእነዚህ አጋላጭ መንስኤዎች አብዛኛዎቹ ሊወገዱ የሚችሉ እንዲሁም ቀድመን በማወቅ እና በመጠንቀቅ መከላከል የሚቻሉ ናቸው ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። ጉበትን በቀላል እና ጤናማ በሆኑ ልምዶች እንዴት ማበረታታት ይቻላል? • በየዕለቱ በቂ ንጹህ ውኃ በመጠጣት፤ • ጤናማ አመጋገብ በመከተል (እንደ ፍራፍሬ፣ አትክልት፣ ጤፍ፣ ባቄላ እና ዓሣ በመመገብ)፤ • ከመጠን በላይ ስብን እና ስኳርን በመቀነስ፤ • አካላዊ እንቅስቃሴን በማዘውተር፤ • አልኮልን በመገደብ ወይም በጭራሽ ባለመጠቀም፤ • የሄፓታይተስ ክትባት በመውሰድ፤ • ያልተረጋገጡ እፅዋትን ከመጠቀም በመቆጠብ፤ • መድኃኒት ከመውሰድ በፊት የጤና ባለሙያ በማማከር እንዲሁም የግል እና የምግብ ንጽህናን በመጠበቅ የጉበትን ጤንነት መጠበቅ ይቻላል ብለዋል ዶክተር አብዲ። ሕክምናውን በተመለከተ o ዶክተር አብዲ እንዳሉት፤ አብዛኛዎቹ የጉበት በሽታዎች ሊታከሙ ይችላሉ፤ በጊዜ ከተደረሰም መቆጣጠር እና መዳን ይችላሉ። o ለሄፓታይተስ ቢ/ሲ ፀረ-ቫይረስ መድኃኒቶች ሕክምና መከታተል፤ o አልኮል መጠጣት በማቆም ጉበት በፍጥነት እንዲያገግም ማገዝ፤ o ለሰባ ጉበት፣ ለስኳር በሽታ እና ለኮሌስትሮል መብዛት በመድኃኒት ማከም፤ o አመጋገብን ማስተካከል፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፤ o የከፋ ደረጃ ላይ የደረሰ ከሆነ እንደደረጃው የተለያዩ ሕክምናዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ እስከ ንቅለ ተከላ ድረስ ሊታከም ይችላል ብለዋል። ጉበት በዓለም አቀፍ ደረጃ…. 👉 በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ 2 ቢሊየን የሚጠጉ ሰዎች እንደ ሄፓታይተስ ቢ እና ሲ ያሉ የጉበት ህመሞች ተጋላጭ ናቸው። ለዚህም ከመጠን በላይ አልኮል መጠጣት፣ ውፍረት እና የስኳር በሽታ በሰፊው በዓለም አቀፍ ደረጃ ብዙዎችን ተጋላጭ ያደርጋሉ ነው ያሉት። 👉 በአፍሪካ ውስጥ ወደ 80 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች ለሄፓታይተስ ቢ በሽታ ተጋላጭነት ውስጥ ይኖራሉ። ከዚህ ውስጥ 60 በመቶው የሚሆነው በክትባት ውስንነት፣ በጤና አጠባበቅ ተደራሽነት እና በአፍላቶክሲን የተበከሉ (እንደ በቆሎ እና ማሽላ ባሉ) ሰብሎች ምክንያት ለአደጋ ተጋላጭ ነው ብለዋል። 👉 በኢትዮጵያም እስከ 7 በመቶ ያህሉ ሕዝብ ለሄፓታይተስ ቢ ተጋላጭ መሆኑን ነው ያመላከቱት። ለዚህም አልኮል አላግባብ መጠቀም፣ ጫት መጠቀም እና የስኳር በሽታ መጨመር ለብዙዎች በተለይም ከ40 ዓመት በላይ ለሆኑ ወንዶች ተጋላጭነትን እንደሚጨምር አስገንዝበዋል። 👉 በአጠቃላይ ክትባት በመውሰድ፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ በመከተል፣ ጤናማ አመጋገብ በማዘውተር ብሎም በወቅቱ በመታከም ተጋላጭነትን በመቀነስ የጉበት ጤንነትን መጠበቅ ይገባል ሲሉ መክረዋል።
አስም-የበርካቶች ሰቀቀን …
Aug 28, 2025 310
በወቅትና የአየር ሁኔታ ሳይገደብ የበርካቶች ስቃይ የሆነውን አስም እንዴት ማከም ይቻላል…? የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • አስም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ፍጹም ገለጻ፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም አስም ይባላል። • የአስም ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው? የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ በአብዛኛው ምልክቶቹ በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ ገልጸዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸው፤ ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር) ብናኝ፣ የእንስሳት ፍግ ሽታዎች አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ያስረዳሉ። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑን አስረድተዋል። • ለአስም ህመም አጋላጭ ወይም ለህመሙ መባባስ መንስኤዎቹ ምንድን ናቸው? አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የአየር ብክለት፣ ጭስ)፤ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ዶክተር ፍፁም ገልጸዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ በቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ ወቅት ሙቀት የሚሰጡ ልብሶችን መልበስ፤ ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። • ሕክምናውስ ምንድን ነው? የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የአየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል።
አሸንዳ- የፍቅርና የሰላም አጀንዳ
Aug 23, 2025 520
በአማረ ኢታይ የሴቶች በተለይም የልጃገረዶች በዓል መሆኑ የሚነገርለት የአሸንዳ በዓል ለማክበር አመቱ እስከሚደርስ ድረስ በጉጉትና በናፍቆት ይጠበቃል። አሸንዳ ይዋቡበታል፣ ቁንጅና ጎልቶ ይወጣበታል፣ ልጃገረዶችና ሴቶች ተሰባስበው የሚያዜሙበት፣ በስጦታ ጭምር የሚታጀብ ልዩ እና ውብ የአደባባይ በዓል ነው። የአሸንዳ በዓል ሲቃረብ በተለይ ልጃገረዶች ቀደም ብለው የመዋቢያ ጌጣጌጦችንና አልባሳትን አዘጋጅተው የበዓሉን መድረስ ይጠባበቃሉ። እለቱም ሲደርስ በተለየ ሁኔታ ተውበውና ደምቀው ከበሮ ይዘውና በጣእመ ዜማ ታጅበው ወደ አደባባይ በመውጣት ያከብሩታል።   በዚህም መሰረት ትግራይ የአሸንዳ በዓል በየዓመቱ ከነሃሴ 16 ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በደማቅ ስነ ስርአት ይከበራል። እለቱ የልጃገረዶች የነፃነት ቀንም በመሆኑ የቤተሰብ፣ የዘመድ አዝማድ ቁጣ እና ይህን አድርጊ ይህን አታድርጊ የሚል ትእዛዝ እና ጫና አይኖርም። በመሆኑም አሸንዳ - የነፃነት፣ የፍቅርና የሰላም አጀንዳ ያነገበ በመሆኑ ከልጅ እስከ አዋቂ በየአመቱ በጉጉት የሚጠበቅ ደማቅ በዓል ነው። የአሸንዳ ልጆች ከበዓሉ ዋዜማ ጅማሮ እስከ ፍጻሜው ድረስ በየሰፈራቸው በቡድን በቡድን ተሰባስበው የሚጫወቱበት በመሆኑም የህብረት፣ የፍቅር፣ የሰላምና የአብሮነት ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል።   ወላጆቻቸው አነስተኛ ገቢ ያላቸው ልጃገረዶችም ከእኩዮቻቸው፣ ከዘመድ አዝማድ እና ከጎረቤቶቻቸው የመዋቢያ ጌጣጌጦችን፣ አልባሳትና ሌሎች ቁሶችን ወስደው በዓሉን በደስታ የሚያሳልፉ ይሆናል። በዚህም መሰረት በዓሉ የመረዳዳት፣ የትብብርና ችግርን በመተጋገዝ ማለፍ እንደሚቻል የሚያመላክት ልዩ በዓል ነው። በዚሁ መሰረት የ2017 ዓ.ም የአሸንዳ በዓል በደማቅ ስነ ስርአት በመከበር ላይ ይገኛል። የፌደራል መንግስት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች፣ በርካታ ቱሪስቶች ልጃገረዶችና ሌሎችም የበዓሉ ታዳሚዎች በተገኙበት በመከበር ላይ ነው። በክብር እንግድነት በመገኘት ንግግር ያደረጉት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፤ ኢትዮጵያ በርካታ ውብ የሆኑ መገለጫዎች ያሏት ሀገር በመሆኗ አጉልተንና ለዓለም አስተዋውቀን የውበታችን ማሳያ እና የሃብት ምንጭ ጭምር ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል። የአሸንዳ በዓልን እሴት በመጠበቅ ለትውልድ ለማስተላለፍ ተቀናጅተን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የሚከበሩ ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶችን በማክበር ጠብቆ ማዝለቁ እንዳለ ሆኖ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን የማልማትና ታሪካዊ ቅርሶችን መጠበቅም ትኩረታችን ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል።   በመጨረሻም የአሸንዳ በዓልን በድምቀት እያከበረ ለሚገኘው ለመላው የትግራይን ህዝብ በተለይም ለልጃገረዶች የሰላምና የፍቅር በዓል እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸውላቸዋል። "የአሸንዳ በዓልን ማስዋብና ማድመቅ ለሰላምና ለአንድነት ያለንን መልካም ፍላጎትና ምኞት ማሳያ ነው። ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና እንዲለማ እንሰራለን።" በማለት መልእክታቸውን ያጋሩት ደግሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ናቸው። በጊዜያዊ አስተዳደሩ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አፅበሃ ገብረእግዛብሄር በበኩላቸው፣ ባህላዊ ይዘት ያለው የአሸንዳ በዓል ሳይበረዝ ትውፊቱን ጠብቆ እንዲቀጥል የክልልና የፌዴራል መንግስታት በጋራ እንሰራለን ብለዋል። በመቀሌ ከተማ እየተከበረ ባለው የአሸንዳ በዓል ከባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ በተጨማሪ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እና ሌሎችም ታድመዋል። አሸንዳ - የነፃነት፣ የፍቅርና የሰላም አጀንዳ ሆኖ መከበሩንም ቀጥሏል።
በሥራ ፈጠራ የስኬት ጉዞ የጀመረው ወጣት ተሞክሮ
Aug 22, 2025 504
(በያንተስራ ወጋየሁ - ከዲላ ኢዜአ ቅርንጫፍ) አንዳንዴ መዳረሻን የሚያሳምረው መነሻችን ነው ሲባል ይደመጣል።መነሻው ጥሩ ከሆነ ኋላ ለሚገኘው ስኬት መደላድል ይሆናል ለማለት ነው። ነገን አርቆ በማሰብና በማለም መስራት የህይወት ጉዞን ቀናና ስኬታማ ለማድረግ ጠቀሜታው የጎላ ነው። የሚገጥም ፈተናን እያሰቡ ወደኋላ ከማለት ይልቅ መፍትሄ በመፈለግ ወደስራ የገቡ ስኬት ሲያስመዘግቡ ይታያሉ። በዚህም ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎችም ወጣቶች ሲተርፉ ይስተዋላል። በፈተና ወደኋላ ሳይል ከችግሩ የሚወጣበትን መንገድ በመፈለግ ስኬት ማስመዝገብ የጀመረው የወናጎ ከተማ ወጣት ኤፍሬም ጴጥሮስ ለእዚህ አንድ ማሳያ ነው። ወጣቱ በከተማው የቱቱፈላ ቀበሌ ነዋሪ ነው። በ2015 ዓ.ም በ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ያመጣው ውጤት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የሚያስገባ አልነበረም። በዚህ ምክንያት ሁለት ዓመታተን እንዲሁ ያለስራ አባክኗል። ያለሥራና ያለትምህርት ባሳለፋቸው ሁለት ዓመታት ድብርት ውስጥ ገብቶ እንደነበር ያስታወሰው ወጣት ኤፍሬም በዚህ ሁኔታ ግን ህይወቱን መቀጠል አልፈለገም። በዙሪያው ለሀብት ምንጭ የሚሆኑ ነገሮችን ትኩረት ሰጥቶ ማሰላሰል ጀመረ። በወናጎ ከተማ ራሱን ከመለወጥ ባለፈ የአካባቢውን ማህበረሰብ መጥቀም የሚችልባቸውን የሥራ አማራጮችን ማየቱን ቀጠለ። በዚህ ወቅት ነበር በአዲስ እሳቤ የተጀመረውና ብዙዎች በስፋት በመሳተፍ ተጠቃሚ እየሆኑበት ያለው የሌማት ትሩፋት መርሀግብር ቀልቡን የገዛው። ይህ ሀገራዊ ኢንሼቲቭ ማህበረሰቡ ያለውን ልምድ የበለጠ በማስፋትና በማዘመን ተጠቃሚ እያደረገው በመምጣቱ የእሱንም ችግር ሊፈታ እንደሚችል ወጣቱ በማመኑ ቀዳሚ ትኩረት ያደረገው የዶሮ እርባታ ሥራ ላይ ነው። መንግስት ለማህበረሰቡ የዶሮ ጫጩቶችን በብዛት ማሰራጨት ተከትሎ ብዙች በዶሮ እርባታ ሥራ ተሰማርተዋል። የወናጎ ከተማ ነዋሪዎችም በዘርፉ ለመሰማራት ባላቸው ከፍተኛ ፍላጎት የዶሮ ጫጩቶችን በብዛት ሲረከቡ በየዕለቱ ማየቱ በውስጡ አንድ ነገር አጫረበት። በከተማው ለብዙ ሰዎች ለዶሮ እርባታ የሚሆን በቂ ስፍራ ማግኘት አዳጋች መሆኑ ለአምራቾች ትልቅ ፈተና ነው። ይህን የተረዳው ወጣቱ ለዚህ ችግር መፍትሄ ሊሆን የሚችል ነገር ቢሰራ አንድም ለራሱ ሥራ መፍጠር ነው፤ በሌላ ቡኩል የነዋሪዎችን ችግር መፍታት መሆኑን አሰበ። በአካባቢው ካሉ ግብአቶች በቀላል ወጪ ለማህብረሰቡ ይጠቅማል ያለውን ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤት ለመስራት ወሰነ። ጉዳዩን ከራሱና ከሌሎች ጋርም መከረበት። በእዚህም ወደስራው ለመግባት የሚያስችል ገንቢ ምክረ ሀሳብ አገኘ። ሀሳቡ አዲስና ለነዋሪውም የሚሰጠው ጥቅም የጎላ መሆኑ ደግሞ ይበልጥ አበረታታው። ይህም ተጨማሪ ብርታት ሆኖት ሀሳቡን ወደድርጊት በመቀየር "ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤት" በመስራት ለሽያጭ ማቅረብ ጀመረ። ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤቱ በጥቂት ቦታ በአንድ ጊዜ 120 የዶሮ ጫጩቶችን ለማርባት የሚያስችልና ሰፊ ቦታ የማይዝ መሆኑም በብዙዎች ዘንድ ተመራጭ እድርጎታል። ‎ወጣት ኤፍሬም በወናጎ ከተማ ያለውን የቦታ ችግር ለመፍታት በአካባቢው ያለን ግብአት ተጠቅሞ የሰራው ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤት ዛሬ ከጌዴኦ ዞንና ወናጎ ከተማ ባለፈ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደረጃ በብዙዎች ዘንድ ተፈላጊ እየሆነ መጥቷል። ከስኬቶቹ መካካል በዚህ ሥራው በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ ተስፋ ሰጪ ለውጥ እያሳየ ነው። የራሱን ሥራ ከፈጠረ ከአንድ ዓመት ያነሰ ጊዜ ቢሆነውም ከራሱና ከቤተሰቦቹ አልፎ ለሦስት የአካባቢው ወጣቶችም የሥራ ዕድል መፍጠር ችሏል። በወር ከአራት በላይ የተንቀሳቃሽ ዶሮ ቤቶችን በመሸጥ ከ100 ሺህ ብር በላይ ገቢ እንደሚያገኝ የሚናገረው ወጣቱ የዶሮ ቤት ሥራውም በህይወቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ ለውጥ እንዲያመጣና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱን እንዳሳደገው ይናገራል። በዚህም ሰርቶ ለመለወጥ ያለው ፍላጎት መነሳሳቱን የገለጸው ወጣቱ ጎን ለጎን የዶሮ እርባታ ሥራ ጀመረ። ተንቀሰቀሽ የዶሮ ቤት አዘገጅቶ ከመሸጥ ባለፈ ለሌሎች አርቢዎች ማስተማሪያ ይሆናል በሚል የ45 ቀን የእንቁላል ጣይ የዶሮ ጫጩቶችን በማርባት ለአካባቢ ማህበረሰብ እያቀረበ ይገኛል። ይህም ሥራውን በመጠንና በአይነት ለማስፋትና ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት አስችሎታል። የለውጡ ምክንያት "በአጭር ጊዜ ላሳየሁት ለውጥ ምክንያቱ ለሥራ ያለኝ ተነሳሽነት ነው" የሚለው ወጣቱ የተጠናከረ የገበያ ትስስርም እንዳለው ተናግሯል። በሚገጥም ችግር ተስፋ መቁረጥ መፍትሄ እንደማይሆን ለሌሎች ወጣቶች ይመክራል። ከዚያ ይልቅ በአካባቢ ያለን ሀብት ለልማት በማዋል ተጠቃሚነትን ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ ነው የገለጸው። በተለይ ኑሮ ለውጥ ለማምጣት በሀገራዊ ኢንሼቲቮች በመሳተፍ ተጠቃሚ ለመሆን ተግቶ መስራት ይገባል ባይ ነው። የወጣቱን የዶሮ ቤት በመጠቀም በዶሮ እርባታ ሥራ ከተሰማሩ የወናጎ ከተማ ወጣቶች መካከል ወጣት አማኑኤል ቦጋለ አንዱ ነው። ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤቱ በውስን ስፍራ ዶሮ የማርባት ፍላጎቱን አሳክቶለታል። ሦስት ካሬ ብቻ የሚይዘውን የዶሮ ቤት በ20 ሺህ ብር በመግዛት በ120 የዶሮ ጫጩቶች ሥራውን ጀምሮ እያከናወነ ይገኛል። በአሁኑ ወቅትም ከራሱ ፍጆታ ባለፈ እንቁላል በመሸጥ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱን ነው የተናገረው። የዶሮ ቤቱ የመመገቢያ፣ የማደሪያና ኩስ መጥሪግያ በዘመናዊ መንገድ የተዘጋጀለት መሆኑ ስራውን በቀላሉ ለማከናውን እንዳስቻለውም ገልጿል። የዶሮ ቤቱ እሱን ጨምሮ ለብዙዎች ከቦታ እጥረት ጋር በተያያዘ የነበረባቸውን ችግር እንደፈታ የገለጸው ወጣቱ፣ በሌማት ትሩፋት የተጀመረው የዶሮ እርባታ ሥራ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ተናግሯል። ይህን የሌማት ትሩፋት ሥራ የሚያጠናክሩ የፈጠራ ሥራዎች ደግሞ ተጠቃሚነትን ይበልጥ ስለሚያሳድጉ መስፋፋት እንዳለባቸውም ነው የተናገረው። በወናጎ ከተማ አስተዳደር ግብርና ዩኒት የእንስሳት ዘርፍ አስተባባሪ ወይዘሮ ፀደይ አጋደ በከተማዋ ከፍተኛ የሰዎች ጥግግት እንዳለ ያነሳሉ። ይሁን እንጂ የአካባቢውን ሀብቶች በመጠቀም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ስራዎች ብዙዎች ተጠቃሚ እየሆኑና ህይወታቸውን እየለወጡ መጥተዋል። ነዋሪውም በዶሮ እርባታ ተሰማርቶ ተጠቃሚ ለመሆን ያለው ፍላጎት ከፍተኛ ነው። የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭን ተከትሎ በዶሮ እርባታ የሚሰማሩ ሰዎች ቁጥር ቢጨምርም የቦታ እጥረት ፈተና ሆኖ መቆየቱን ያነሳሉ። የህብረተሰቡን የቦታ ጥያቄ መፍታት ለአስተዳደሩ መሰረታዊ ተግዳሮት እንደነበር አስታውሰው፤ ወጣት ኤፍሬም በአካባቢ ከሚገኝ ግብዓት ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤት ስርቶ ለሽያጭ ማቅረቡ ችግሩን እያቀለለው መሆኑን ይናገራሉ። ወይዘሮ ፀደይ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት በከተመው በሦስት የዶሮ መንድሮች የዶሮ እርባታ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። በዚህም 14 በማህበር የተደራጁ እና ከ80 በላይ በግል የተሰማሩ ዶሮ አርቢዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው። የልማት ሥራው እንቁላልና ዶሮ ለማህበረሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እያስቻለ ነው። በወጣቱ የተሰራው ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤትም ከቦታ ጥበት ጋር በተያያዘ ከነዋሪዎች ሲነሳ የነበረውን ጥያቄ እየፈታ መሆኑን አስተባባሪዋ ይገልጻሉ። እንደወጣት ኤፍሬም የዜጎችን ችግር የሚፈቱና በመንግስት የሚከናወኑ የልማት ተግባራትን የሚያግዙ ፈጠራ የታከለባቸው ሥራዎች ልማቱ የበለጠ ስለሚያጠናክሩ የሚደገፉና የሚበረታቱ መሆናቸውን ነው የገለጹት። በየአካባቢው ያልተነኩ ሀብቶች አሉ። ዋናው ነገር ግን እነዚህን ሀብቶች እንዴት ወድልማት በመቀየር ተጠቃሚ መሆን ይቻላል የሚለው ነው። በተለይ ወጣቶች ሥራ የለም በሚል ምክንያት የማይተካ ጊዜን ያለአግባብ ማሳለፍ አይገባም። ህገወጥ ስደትን ምርጫ ማድረግም አግባብ እንዳልሆነ የወጣት ኤፍሬም ተሞክሮ እንድ ማሳያ ነው። መንግስት የዜጎችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የተለያዩ ኢኒሸቲቮችን ቀርጾ ወደተግባር አስገብቷል። በእነዚህ ኢኒሼቲቮች መሳተፍና እንዴት ስኬታማ መሆን እንደሚችሉ ቆም ብሎ ማሰብ ብቻ ነው ከእነሱ የሚጠበቀው። ያኔ መዳረሻቸውን አርቀው ማለም ይጀምራሉ። መነሻቸው መሰረት ከያዘ መዳረሻቸውን ማሳመር ይችላሉና ከወናጎ ከተማ ወጣት ኤፍሬም የስኬት ጉዞ ትምህርት መውሰድ ይገባል።    
ትንታኔዎች
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 957
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 1260
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 4432
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 3903
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 4204
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 3307
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 4819
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 51043
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 48374
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 29374
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 26820
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 24595
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 22721
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 22681
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 22335
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 51043
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 48374
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 29374
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 26820
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል አብዮት
Aug 27, 2025 467
በሙሴ መለስ/ኢዜአ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል ዋንኛ ማዕከል በመሆን ላይ ትገኛለች። የተፈጥሮ ውበቷን ከኢኖቬሽን ጋር በማስተሳሰር የአየር ንብረትን የማይበክሉ የተለያዩ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን እየተጠቀመች ይገኛል። አዲስ አበባ ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን እየተጠባበቀች ነው። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ስራ በጉባኤው ከምታቀርባቸው ተሞክሮዎች መካከል ይጠቀሳል። ኢትዮጵያ ከውሃ፣ ከፀሐይ፣ ከነፋስ፣ ከእንፋሎት ሃይል፣ ባዮማስ ከእንስሳትና እጽዋቶች ተረፈ-ምርት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አላት። ይህም የሚያሳየው አብዛኛውን የኤሌክትሪክ ኃይል የምታገኘው ከታዳሽ የኃይል ምንጮች መሆኑን ነው። ኢትዮጵያ ከጂኦተርማል 10 ሺህ ሜጋ ዋት ከንፋስ ኃይል ደግሞ 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት እምቅ አቅም አላት። ግንባታው የተጠናቀቀው እና 5 ሺህ 200 ሜጋ ዋት የሚያመነጨው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም ከብክለት ነጻ የኃይል ምንጭ ከመሆን ባለፈ ለሀገሪቷ ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። መንግስት የሀገሪቱን የኃይል እጥረት ለመቅረፍ በዋና ዋናዎቹ የወንዞች ተፋሰሶች የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክቶችን በማልማት ላይ ይገኛል። በ10 ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅዷ ኢትዮጵያ የምታመነጨውን የኃይል መጠን አሁን ካለበት 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ ግብ ተቀምጧል። የተሻሻለው የኢነርጂ ፖሊሲዋም ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ነባራዊ ዕውነታ መሰረት ያደረገ እና ጎረቤት ሀገራትን በኃይል መሰረተ ልማት ለማስተሳሰር ያለመ ነው። ይህንንም እውን ለማድረግ በመንግስት ከሚለሙት የኃይል ምንጮች በተጨማሪ በግሉ ዘርፍ ኃይል ተመርቶ የኃይል አቅርቦቱ እንዲሻሻልና ዘላቂ እንዲሆን አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ ይህንንም እውን ለማድረግ በ2009 ዓ.ም በገንዘብ ሚኒስቴር ስር የመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት ፕሮጀክት በአዋጅ ቁጥር 1076/2018 ተመስርቷል። በዚህ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት ስምንት የፀሐይ ኃይል፣ አምስት የሃይድሮ ኤሌክትሪክ እና አምስት የንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶችን ለማልማት እየተሰራ ይገኛል። ከስምንቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች እስከ 750 ሜጋ ዋት ኃይል ለማግኘት መታቀዱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መረጃ ያመለክታል። ጋድ 1 እና 2፣ ዲቼቶ፣ ወራንሶ፣ ሁመራ፣ ወለንጪቲ፣ መቀሌ፣ ሁርሶ እና መተማ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶቹ ናቸው። አዳማ አንድ፣ አዳማ ሁለት፣ አይሻ ሁለት እና አሸጎዳ ከንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶቹ መካከል ይጠቀሳሉ። የእንፋሎት (ጂኦተርማል) ኃይልን በተመለከተም በመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት ፕሮጀክት ኮርቤቲ ከሚባል የግል አልሚ ጋር መንግስት ተዋውሎ ድርጅቱ የሚያመርተውን 150 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢትዮጵያ ለማቅረብ እየሰራ ይገኛል። በአጠቃላይ በተለያዩ የኢነርጂ አማራጮች የኢትዮጵያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ሽፋንን 54 በመቶ ማድረስ መቻሉን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም አማካኝነት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2030 65 በመቶ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከብሔራዊ የኃይል ቋት እንዲሁም ቀሪው 35 በመቶ ከኃይል ቋት ውጭ ባሉ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ የማድረግ እቅድ ተይዟል። ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለምስራቅ አፍሪካ ሀገራት እያቀረበች ያለው አረንጓዴ የኃይል አማራጭ የአየር ንብረት ተጽእኖን ለመከላከል እና ከባቢ አየርን ለመጠበቅ ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው። የተሻሻለው የኢነርጂ ፖሊሲዋም ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ነባራዊ ዕውነታ መሰረት ያደረገ እና ጎረቤት ሀገራትን በኃይል መሰረተ ልማት ለማስተሳሰር ያለመ ነው። በርግጥ ከሕዳሴው ግድብ ባሻገር ሌላው ከአፍሪካ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው የኮይሻ ኃይል ማመንጫም ለቀጣናዊ ትስስር መፋጠን ሌላው እድል ነው። በጥቅሉ ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገራት የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል የሀገራት ኢኮኖሚ ትብብር የሚያጠናክር እና የኢትዮጵያን የመሰረተ ልማት የማስተሳሰር ጽኑ ፍላጎት ማሳያ ነው። በተጨማሪም በቀጣናው ዘላቂ የኤሌክትሪክ ገበያ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ክፍለ አሕጉራዊ ጥረት ነው። ጥረቱ የምሥራቅ አፍሪካ የሃይል ቋት (The Eastern Africa Power Pool-EAPP) በቀጣናው ሀገራት መካከል ድንበር ተሻጋሪ የሃይል ንግድ እና የሃይል መስመር ትስስርን ለማሳለጥ እኤአ በ2005 የተቋቋመ ተቋም ግብ እውን ከማድረግ ባለፈ አሕጉራዊ ምጣኔ ሃብታዊ ትስስርን ያፋጥናል። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኢነርጂ አብዮት የአየር ንብረት ለውጥ የመከላከል ስራ እና የደን ልማትን የሚያግዝ ነው። ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ እየተቃረበ ባለበት ወቅት ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኃይል አሻራውን ለአፍሪካ ለማሳየት ተዘጋጅታለች። አረንጓዴ የኃይል አማራጮች ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት የማይበገር ኢኮኖሚ መገንቢያ ዋና ምሰሶዎች መካከል ይጠቀሳል።
የኢትዮጵያ የካርቦን ገበያ፤ፍትሃዊ የአየር ንብረት ፋይናንስ አቅርቦት ማግኛ አማራጭ ---
Aug 26, 2025 483
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፤ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። ከጉባኤው አጀንዳዎች መካከል የአፍሪካ የካርቦን ሽያጭ ይገኝበታል። የካርቦን ንግድ ማለት የካርቦን ዳይኦክሳይድ እና ሌሎች የአየር ንብረት ለውጥን የሚያስከትሉ ጋዞችን ልቀትን ለመቆጣጠር የሚደረግ የገበያ ዘዴ ነው። ልክ እንደ ሌሎች ምርቶች ሁሉ የካርቦን ልቀትን የመገበያያ ዕቃ አድርጎ ይቆጥረዋል። መንግስታት ወይም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ኩባንያዎች ወይም ተቋማት ሊለቁት የሚችሉትን ከፍተኛውን የካርቦን መጠን ይወስናሉ።ይህ መጠን “የልቀት ጣሪያ” (Emission Cap) ይባላል። ከዚያም እያንዳንዱ ኩባንያ ይህን ያህል ካርቦን የመልቀቅ “ፈቃድ” ወይም “ክሬዲት” (Credit) ይሰጠዋል። ካርቦን ክሬዲት፦ ኩባንያዎች እንደ ደን ልማት ወይም የታዳሽ ኃይልን በመሳሰሉ ፕሮጀክቶች ላይ ኢንቨስት በማድረግ ብድር የሚያገኙበት ስርአት ነው። የካርቦን ንግድ ሀገራት፣ኩባንያዎች እና ግለሰቦች በተገዢነት እና በፈቃደኝነት ላይ ተመስርተው የሚያከናወኑት ነው። አፍሪካ በዓለም ደረጃ ወደ ከባቢ አየር በሚለቀቀው በካይ ጋዝ ልህቀት ከአራት በመቶ ያነሰ ድርሻ ቢኖራትም የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ዳፋ ተሸካሚ አህጉር ሆናለች። የካርቦን ገበያ ለአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ ለስራ እድል እና ለብሄራዊ አየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች ትግበራ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የአፍሪካ ሀገራት በ2015 ዓ.ም በግብጽ ሻርም አል ሼክ በተካሄደው 27ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንበረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-27) የአፍሪካ ካርቦን ገበያ ኢኒሼቲቭ ይፋ አድርገዋል። በኢኒሼቲቩ አማካኝነት አፍሪካ በዓመቱ በ300 ሚሊዮን የካርቦን ክሬዲት ስድስት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዳለች። እ.አ.አ በ2030 በካርቦን ንግድ ለ30 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር ውጥን ተይዟል። የካርቦን ገበያ በአፍሪካ ሀገራት ተስፋ ሰጪ እድገት እያሳየ ይገኛል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ኬንያ፣ ጋና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሩዋንዳ እና ሴኔጋል የካርቦን ገበያ የአሰራር ማዕቀፎችና ግቦች አዘጋጅተው እየሰሩ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክም የካርቦን ገበያ የፋይናንስ አማራጭ በማዘጋጀት ሀገራት ማዕቀፎች እንዲቀርጹና የካርቦን ክሬዲት በአፍሪካ የአክሲዮን ገበያዎች ውስጥ እንዲካተቱ አድርጓል። የአፍሪካ ሕብረት የልማት ኤጀንሲ (አውዳ-ኔፓድ) በአህጉሪቷ የካርቦን ገበያ ቀረጻ፣ ትግበራ እና የግብይት ስርዓቱን የሚወስን “African Gold Standard” የተሰኘ የአሰራር ማዕቀፍ አዘጋጅቶ እየተገበረ ይገኛል። ማዕቀፉ የካርቦን ገበያ ማህበረሰቦች ካርቦንን በማመቅ ስራቸው ተጨባጭ ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥና ለብዝበዛ እንዳይጋለጡ ክትትልና ድጋፍ የሚደረግበት መንገድ ነው። የአየር ንብረት ጉባኤውን የምታዘጋጀው ኢትዮጵያ በካርበን ገበያ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኢትዮጵያ ሙቀት አማቂ ጋዞች ልቀት ቅነሳና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ ቀርጻ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ እንደሆነች የፕላንና ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። የእርምጃዎቹ አንድ አካል የሆነው የካርቦን ግብይትን በውጤታማነት ለመምራትና ተጠቃሚ ለመሆን ብሔራዊ የካርበን ግብይት ስትራቴጂ አዘጋጅታለች። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የካርቦን ግብይት ስትራቴጂ የመጨረሻ ረቂቅ ግምገማ እና የካርቦን ገበያ የህግ ማዕቀፍ የህግ ክፍተት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት (Validation Worksop on draft Ethiopia’s National Carbon Market Strategy and Consultation on the Legal Gap Analysis Report) ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በግንቦት ወር 2017 ዓ.ም በቢሾፍቱ አካሄዶ ነበር። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን ስትራቴጂውን በፍጥነት ወደ ስራ ለማስገባት ከስትራቴጂ ዝግጅቱ ጎን ለጎን የካርቦን ገበያ ሊመራበት የሚችል የህግ ማእቀፍ ለማዘጋጀት የህግ ክፍተት የዳሰሳ ጥናት መካሄዱን ገልጸዋል። የማዕቀፉ ዓላማ በኢትዮጵያ በአግባቡ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል የህግ ማዕቀፉን በፍጥነት አዘጋጅቶ በማጸደቅ የካርቦን ግብይት ላይ በንቃት እና የኢትዮጵያን ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መልኩ መሳተፍ እንደሆነ ተናግረዋል። በመድረኩ ላይ የካርቦን ገበያ ልማት ስትራቴጂ ረቂቅ ሰነድ እና የካርቦን ገበያ ንግድ የህግ ማዕቀፍ ዳሰሳ ጥናት ሰነድ ግብአቶችን አካቶ በማዳበር ያሉትን ሂደቶች በማለፍ በቅርብ ጊዜ ወደ ስራ እንዲገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል። ብሔራዊ የካርቦን ገበያ ሽያጭ ስትራቴጂ መዘጋጀቱ ኢትዮጵያ በደን ልማት፣በትራንስፖርት፣ በቆሻሻ አወጋገድና በኃይል አማራጭ ልማት ላይ በምታበረክተው ልክ ተጠቃሚ የሚያደርጋት መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል። በዚህም ሙቀት አማቂ ጋዞችን በመቀነስ፣ አረንጓዴ ኢኮኖሚ በማሳለጥና የዜጎችን ተጠቃሚነት በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራን ለማገዝ ጉልህ ፋይዳ ያለው መሆኑን አመልክቷል። ኢትዮጵያ ከኖርዌይ በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም የተፈራረመችው የ75 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የካርቦን ሽያጭ ስምምነት በካርቦን ግብይቱ እያገኘች ያለውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያሳይ ነው። እ.አ.አ እስከ 2026 ድረስ የሚቆየው ስምምነት ከካርበን ሽያጭ የሚገኘውን ገቢ እንደ ሀገር የተሰሩ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ለማጠናከር እንዲሁም አዳዲስ የደን ልማት ስራዎችን ለመስራት ይውላል። በባሌና ምዕራብ አርሲ ጥብቅ ደኖች ሲተገበር በቆየው የበካይ ጋዞች ቅነሳና የደን ጭፍጨፋን የመቀነስ ፕሮጀክት (ሬድ ፕላስ) አማካኝነት እየተከናወነ ያለው የካርቦን ንግድ በሚሊዮኖች ብር የሚቆጠር ብር ገቢ እየተገኘበት ነው። ፕሮጀክቱ በመተግበሩ ጉዳት ይደርስበት የነበረው የደን ሀብት መጠበቅ እና የካርቦን ጋዝ ልቀትን ማስቀረት ተችሏል። ኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ የካርቦን ገበያ ተጠቃሚነቷን ለማሳደግ በሀገሪቷ የተለያዩ ጥብቅ ደኖች ካርቦኖችን በማከማቸት ገቢ እንዲገኝ እየሰራች ነው። የካርቦን ግብይት የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ የማግኘት አማራጭ በማስፋት ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት እና የካርቦን ገበያ የአሰራር ማዕቀፍ በመዘርጋት እያከናወነች ያለው ስራ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው። በሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤም በካርቦን ገበያ ያላትን ተሞክሮ ታቃርባለች ተብሎ ይጠበቃል። በጉባኤው ላይ የካርቦን ገበያ የበካይ ሀገራት እና ኩባንያዎች የገንዘብ መክፈያ ዘዴነት ወጥቶ በአፍሪካውያን ባለቤትነት እንዲመራ መሪዎች ጠንካራ ጥሪ እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል። አፍሪካ በጉባኤው ላይ ጠንካራ የካርቦን ገበያ አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣የካርቦን ክሬዲት ሽያጭ ላይ የሚያጋጥሙ የክፍያ ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ማድረግ፣ የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን የበለጠ ማረጋገጥ፣ ተጠያቂነትን ማስፈን እና ፍትሃዊ ገቢ ማግኘት ላይ ለውጥ የሚያመጡ ውሳኔዎችን ማሳለፍ እንዳለባቸው የዘርፉ ባለሙያዎች ይመክራሉ። የካርቦን ገበያ በተገቢው ሁኔታ የሚፈጸም እና የአፍሪካን ባለቤትነት የሚያረጋግጥ ከሆነ ለአህጉሪቷ ዘላቂ የፋይናንስ አማራጭ፣ አይበገሬነትን ለመገንባት እና ዘላቂ እድገትን ለማምጣት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም