ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ሊጠናከር ይገባል
Jun 25, 2026 18
ጋምቤላ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ መሳካት፣ የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሯን ጨምሮ የክልልና የፌደራል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ በአቦቦ ወረዳ በሩዝ ሰብል ላይ እየተካሄደ ያለውን የምርምር ሥራ ዛሬ ጎብኝተዋል። ርዕሰ መስተዳድሯ በወቅቱ እንዳሉት፤ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚቻለው የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋትና ተደራሽ ማድረግ ሲቻል ነው። ክልሉ ያለውን ሰፊ የመሬትና የውኃ ሀብት በምርምር መደገፍ ከተቻለ፣ ለአካባቢው ብቻ ሳይሆን ለሀገር የሚተርፍ የሰብል ምርት ማግኘት እንደሚቻልም ተናግረዋል። ጋምቤላ ለሁሉም የግብርና ልማት ዓይነቶች ምቹ ሥነ-ምህዳር ያላት መሆኑን የጠቀሱት ወይዘሮ ዓለሚቱ፤ በተለይም የሩዝ ሰብል አዋጭ ተብለው ከተለዩት የሰብል ዓይነቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ የሩዝ ልማትን ማዘመንና ማስፋፋት ከተቻለ ለአገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ የሚተርፍ ምርት ማግኘት እንደሚቻልም አክለዋል። ልማቱን ለመደገፍ በባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲና በቻይናው ዩናን ዩኒቨርሲቲ ቅንጅት እየተካሄደ ያለው የምርምር ሥራ የሚበረታታ መሆኑን በመግለጽ፣ ለሥራው ስኬታማነት የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር የታለመውን የግብርና ልማት ስኬታማ ማድረግ የሚቻለው አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለአርሶ አደሩና ለባለሀብቱ ተደራሽ ማድረግ ሲቻል መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በተለያዩ ተቋማት ትብብር በሩዝ ሰብል ላይ የተጀመረው የምርምር ሥራ ተስፋ ሰጪና ዘርፉን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ በበኩላቸው፤ የምርምር ሥራው እየተካሄደ ያለው ከቻይናው ዩናን ዩኒቨርሲቲ ጋር መሆኑን አስረድተዋል። የአዲሱ የሩዝ ዝርያ ልዩ ባህሪያት መካከል በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚደርስ መሆኑ እንዲሁም በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ መመረቱ እንደሆነ ገልጸዋል። በሩዝ ዝርያዎቹ ላይ እየተካሄደ ያለው የማላመድ የምርምር ሥራ በሚቀጥለው ዓመት ተጠናቆ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እንደሚሆንም ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።
በትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ላይ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
Jun 25, 2026 41
ድሬዳዋ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ የትምህርትን ጥራትና ፍትሃዊ ተደራሽነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ አበረታች ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ። በድሬዳዋ አስተዳደር ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ስምንት የቅድመ መደበኛ፣ የሞዴልና የአዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ዛሬ ተጀምሯል። በአስተዳደሩ በ18 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፉትን ትምህርት ቤቶች ግንባታ ያስጀመሩት የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልዪ ናቸው። ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ በወቅቱ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በትምህርት ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙት ውጤታማ ተግባራት የትምህርት ፍትሃዊ ተደራሽነትና ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ውጤት እያሳዩ ናቸው። በተለይም በቅድመ መደበኛ ትምህርት፣ በትምህርት ቤቶች ምገባ እና በሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ላይ የተከናወኑ ተግባራት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት በተግባር ማረጋገጥ ማስቻላቸውን አንስተዋል። ከለውጡ በፊት በመላው ሀገሪቱ 4ሺህ 100 የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች እንደነበሩ አስታውሰው ከለውጡ በኃላ በገጠርና በከተማ 34 ሺህ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው ህፃናት ትምህርትን በጥራት እንዲማሩ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል። ዛሬ በድሬዳዋ የተጀመሩት የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በሀገሪቱ 726 ወረዳዎች ተጨማሪ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት በመጪው የትምህርት ዘመን አገልግሎት እንዲጀምሩ ይደረጋል ብለዋል። እንደ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ገለፃ ስምንት ሚሊዮን ህፃናትን ተጠቃሚ ያደረገው የትምህርት ቤት ምገባ ሀገራዊ መርሃ ግብርም ህፃናት ከትምህርት ገበታ እንዳይለዩና ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ አስችሏል። ዛሬ በድሬዳዋ በ606 ሚሊዮን ብር ግንባታው የተጀመረውና በአንድ ዓመት የሚጠናቀቀው የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትም የትምህርት ጥራትን የማረጋገጥ ጉዞ የሚያጠናክር ይሆናል ብለዋል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር በበኩላቸው፤ የትምህርት ሚኒስቴር በድሬዳዋ ዛሬ መገንባት የጀመራቸው ትምህርት ቤቶች የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊ ተደራሽነትን ይበልጥ ለማሳደግ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ገልጸዋል። ፕሮጀክቶቹን በባለቤትነት በመከታተልና በመደገፍ በተያዘላቸው ጊዜ፣ በጀትና ጥራት እንዲጠናቀቁ አስተዳደሩ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አስታውቀዋል ። ዘመናዊና ሞዴል ፕሮጀክቶቹ በድሬዳዋ የትምህርት ጥራትን እና ተሳትፎን ለማረጋገጥ የተጀመሩትን ስራዎች በላቀ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚያስችሉ የተናገሩት ደግሞ የአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልዪ ናቸው። በትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራው ቡድን ከግንባታ ማስጀመር ጎን ለጎን የድሬዳዋን የትምህርት ቤቶች ምገባ ማብሰያ ማዕከልና ለምገባው መርሃግብር የተዘጋጀውን 18 ሄክታር የፍራፍሬና የአትክልት ማልሚያ ስፍራን ተመልክተዋል።
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ባህል ወደ አዲስ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ
Jun 25, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ባህል ወደ አዲስ ምዕራፍ እንዲሸጋገር እየተደረገ መሆኑን በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ 42 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በርካታ ሚሊዮን ዜጎች በድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ የተሳተፉበት ታሪካዊ ምርጫ ሆኖ ተጠናቋል። የአፍሪካ ህብረት፣ የኢጋድ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና በርካታ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችም የምርጫውን ሂደት ነጻ፣ ፍትሐዊነትና ገለልተኝነት እማኝነታቸውን በመስጠት አረጋግጠዋል። በምርጫው ዕለትም ዜጎች ከማለዳው 10 ሰዓት እስከ እኩለ ሌሊት ድርስ በመሰለፍ ጭምር ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት አስመስክረዋል። በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲዎችና የፖሊሲ ብቻ ሳይሆን የሥርዓት ምርጫ ጭምር ነው። የዴሞክራሲ ተቋማትና ሉዓላዊ የሥልጣን ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃና ገለልተኛነታቸውን በተግባር ያረጋገጡበት ምርጫ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን እውነተኛ ዴሞክራሲ መሻታቸውን ለወዳጅም ለጠላትም ያሳዩበት መሆኑን ገልጸው፤ ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ የተዋንያን ቅንጅት መንጸባረቁንም አድንቀዋል። ምርጫው ከፖለቲካ ፓርቲዎች ውድድር ባለፈ ብሔራዊ ክብርና ሉዓላዊነት የተንጸባረቀበት በመሆኑ ኢትዮጵያ አሸንፋለች ብለዋል። ከለውጡ ማግስት የተደረገው መጠነ ሰፊ የፖለቲካ ሪፎርም የፓርቲዎችን እንግልትና ስደት በማስቀረት ጤናማ የፖለቲካ የፉክክር ምኅዳር መፈጠሩን ገልጸዋል። የሕግና ፖሊሲ ማሻሻያም በስድስተኛውና በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲዎችን ተሳትፎ በማሳደግ አዲስ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ እንዲወለድ ማድረጉን አስረድተዋል። ይህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የሥልጣን ምንጭ ከህዝብ የሚሰጥ ድምፅ መሆኑን በመገንዘብ በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ የሚጠበቅባቸውን ገንቢ ሚና የሚወጡበትን ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም የፖለቲካ ፓርቲዎች የውስጥና የውጭ ጫናን በመቋቋም ጭምር ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ አሻራቸውን ላሳረፉ አካላት ምሥጋና አቅርበዋል። የለውጡ መንግሥት በሀገራዊ የጋራ ጥቅሞች ላይ ከፉክክር ይልቅ በትብብር ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ሥርዓት በመዘርጋት በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በብሔራዊ ጥቅም ላይ ወጥ የሆነ አቋም እንዲይዙ አድርጓቸዋል ብለዋል። ይሄ ትልቅ የዴሞክራሲ ትሩፋት መሆኑን በማንሳት፤ ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው በፓርቲዎች መካከል መተማመን በመፍጠር የኢትዮጵያን መዳከም የሚሹ ኃይሎችና ታሪካዊ ጠላቶችን ማሳፈሩን ገልጸዋል።
ሀገራት ከፍተኛ የገንዘብ መጠን የሚያጋብሱበት የዓለም ዋንጫ ክብረ ወሰን ሽልማት
Jun 25, 2026 51
በሙሴ መለሰ 23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጣምራ አዘጋጅነት መካሄድ ጀምሯል። የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ በበርካታ ነገሮች «የመጀመሪያ» የተሰኙ አዳዲስ ነገሮችን ይዟል። ከነዚህም መካከል ለውድድሩ ተሳታፊ ሀገራት የሚበረከተው የገንዘብ ሽልማት ነው። የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ለዓለም ዋንጫው ተሳታፊ ሀገራት 871 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ሽልማት ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል። ይህም በውድድሩ የ96 ዓመታት ታሪክ ከፍተኛ የሚባለው ነው። የፊፋ ምክር ቤቱ እ.አ.አ ዲሴምበር 2025 በኳታር ዶሃ ባካሄደው ስብሰባ፤ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ለሚሳተፉ አገራት የሚከፋፈል የ727 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ታሪካዊ በጀት አጽድቆ ነበር። ይህ መጀመሪያ ላይ የጸደቀው የገንዘብ መጠን፣ በኳታር አስተናጋጅነት ከተካሄደው የ2022 የዓለም ዋንጫ ጋር ሲነጻጸር የ50 በመቶ ብልጫ ያለው እንደነበር ተገልጿል። በዚሁ የኳታር ስብሰባ ላይ በጸደቀው ስሌት መሠረት፣ የውድድሩ ሻምፒዮን (ባለድል) 50 ሚሊዮን ዶላር ሲያገኝ፣ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ የሚያጠናቅቀው ቡድን 33 ሚሊዮን ዶላር፣ ሦስተኛው 29 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም አራተኛ ደረጃን የሚያገኘው 27 ሚሊዮን ዶላር ተመድቦለታል። በተመሳሳይ ከ5ኛ እስከ 8ኛ ደረጃ የሚይዙት 19 ሚሊዮን ዶላር፣ ከ9ኛ እስከ 16ኛ ደረጃ ላይ የሚቀመጡት 15 ሚሊዮን ዶላር፣ ከ17ኛ እስከ 32ኛ ደረጃ ያላቸው ቡድኖች 11 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ከ33ኛ እስከ 48ኛ ደረጃ ይዘው የሚያጠናቅቁት አገራት እያንዳንዳቸው 9 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት ገንዘብ ያገኛሉ። በተጨማሪም በእያንዳንዱ ደረጃ ላይ ለሚገኙት ቡድኖች ከሚሰጠው የሽልማት ገንዘብ ውጪ፣ ለእያንዳንዱ ተሳታፊ አገር ለዝግጅት ወጪ (Preparation costs) 1.5 ሚሊዮን ዶላር ተመድቦ የነበረ ሲሆን፤ በዚህም ማንኛውም ተሳታፊ አገር ቢያንስ 10.5 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቱ ተረጋግጦ ነበር። ነገር ግን ምክር ቤቱ ውድድሩ ከመጀመሩ 44 ቀናት በፊት፣ እ.አ.አ ኤፕሪልክ 2026 በቫንኩቨር ካናዳ ባደረገው ሌላኛው ስብሰባው ተጨማሪ ማሻሻያ አድርጓል። ውድድሩ ባስመዘገበው ከፍተኛ የንግድ ገቢ ምክንያት፣ ምክር ቤቱ ቀደም ሲል አጽድቆት በነበረው በጀት ላይ ተጨማሪ የ15 በመቶ ጭማሪ በማድረግ አጠቃላይ ድምሩን ወደ 871 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ አድርጎታል። በዚህ የቫንኩቨር ስብሰባ በተወሰነው አዲስ ማሻሻያ መሠረት፦ ለእያንዳንዱ አገር የሚሰጠው የዝግጅት ወጪ (Preparation money) ከ1.5 ሚሊዮን ዶላር ወደ 2.5 ሚሊዮን ዶላር እንዲያድግ ተደርጓል። ለውድድር ተሳትፎ (Qualification money) ከ9 ሚሊዮን ዶላር ወደ 10 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ብሏል። ይህም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ 48 አገራት በሚሳተፉበት በዚህ የዓለም ዋንጫ ላይ የሚሳተፍ ማንኛውም አገር፣ ከምድብ ማጣሪያው ባያልፍ እንኳ በትንሹ 12.5 ሚሊዮን ዶላር (የ2.5 ሚሊዮን ዝግጅት እና የ10 ሚሊዮን የተሳትፎ ክፍያ) ያገኛል። በተጨማሪም ለቡድኖች ልዑካን ቡድን ወጪ መሸፈኛ እና ለትኬት ድልድል ከ16 ሚሊዮን ዶላር በላይ ተጨማሪ ድጎማ መመደቡ ተገልጿል። የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በጉዳዩ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ ፊፋ በአሁኑ ወቅት በታሪኩ እጅግ ጠንካራ በሆነ የፋይናንስ አቋም ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ ይህም ሁሉንም አባል ማኅበራት ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ለመደገፍ እንዳስቻለ ገልጸዋል። ይህ ውሳኔም የፊፋ ሀብት እንዴት በቀጥታ ወደ እግር ኳሱና ለዘርፉ ዕድገት መልሶ ጥቅም ላይ እንደሚውል የሚያሳይ ትልቅ ማረጋገጫ ነው ብለዋል። ከተሳታፊ ቡድኖች ክፍያ የተረፈው አጠቃላይ ገቢ፣ በ211 የፊፋ አባል ማኅበራት አማካኝነት ለዓለም እግር ኳስ ዕድገት ማስፈጸሚያ በድጋሚ ጥቅም ላይ እንደሚውል ፊፋ አስታውቋል።
በዞኑ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉትን ችግኞች የመንከባከብ ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል
Jun 25, 2026 82
ግምቢ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):-በምዕራብ ወለጋ ዞን በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉትን ችግኞች ለመንከባከብ ስራ ትኩረት መሰጠቱን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ። የምዕራብ ወለጋ ዞን አመራሮች እና የዞኑ ነዋሪዎች የተሳተፉበት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በመንዲ ከተማ ዛሬ ተጀምሯል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፈ እንዳሉት፤ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄን ስኬታማ ለማድረግ የተተከሉ ችግኞችን በአግባቡ መንከባከብ ከሁሉም ይጠበቃል። ለመርሃ ግብሩ ስኬታማነትም እንደ ዞን በቂ የችግኝ ዝግጅት፣ ተገቢው የቦታ መረጣ እና የችግኝ መትከያ ጉድጓድ መቆፈሩን ገልጸዋል። በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከተዘጋጁት 328 ሚሊዮን ችግኞች ውስጥ ለምግብነት እና ለገቢ ምንጭ የሚያገለግሉ የፍራፍሬ፣ የቡና እና የእንስሳት መኖ ችግኞች ከፍተኛ ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን አቶ ተሊላ አስገንዝበዋል። ባለፉት ዓመታት በመርሃ ግብሩ የተተከሉ ችግኞች አብዛኛዎቹ ጸድቀው ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ማስገኘታቸውንም ዋና አስተዳዳሪው አረጋግጠዋል። ከመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች መካከል አባገዳ አምቢሳ ሊካሳ በሰጡት አስተያየት፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን እንደ ሰው ልጅ ተንከባክቦ ማሳደግ የትውልዱ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል። በየዓመቱ አሻራቸውን በማኖራቸው ልዩ ደስታ እንደሚሰጣቸው ገልጸው፣ ችግኞችን ከመትከል ባሻገር የጽድቀት ሂደታቸውን በአግባቡ እንደሚከታተሉም ተናግረዋል። አቶ ኤሊያስ ቱቾ በበኩላቸው፤ ችግኝ መትከል በርካታ ጠቀሜታ እንዳለው በመገንዘብ በችግኝ ተከላው እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በየዓመቱ በችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የተናገረው ደግሞ ወጣት ኩርፈሳ ኦልጂራ ነው። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ከ200 በላይ የፍራፍሬ ችግኞችን በግሉ ለመትከል ማቀዱንም ጠቁሟል።
ፖለቲካ
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ባህል ወደ አዲስ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ
Jun 25, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ባህል ወደ አዲስ ምዕራፍ እንዲሸጋገር እየተደረገ መሆኑን በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ 42 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በርካታ ሚሊዮን ዜጎች በድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ የተሳተፉበት ታሪካዊ ምርጫ ሆኖ ተጠናቋል። የአፍሪካ ህብረት፣ የኢጋድ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና በርካታ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችም የምርጫውን ሂደት ነጻ፣ ፍትሐዊነትና ገለልተኝነት እማኝነታቸውን በመስጠት አረጋግጠዋል። በምርጫው ዕለትም ዜጎች ከማለዳው 10 ሰዓት እስከ እኩለ ሌሊት ድርስ በመሰለፍ ጭምር ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት አስመስክረዋል። በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲዎችና የፖሊሲ ብቻ ሳይሆን የሥርዓት ምርጫ ጭምር ነው። የዴሞክራሲ ተቋማትና ሉዓላዊ የሥልጣን ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃና ገለልተኛነታቸውን በተግባር ያረጋገጡበት ምርጫ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን እውነተኛ ዴሞክራሲ መሻታቸውን ለወዳጅም ለጠላትም ያሳዩበት መሆኑን ገልጸው፤ ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ የተዋንያን ቅንጅት መንጸባረቁንም አድንቀዋል። ምርጫው ከፖለቲካ ፓርቲዎች ውድድር ባለፈ ብሔራዊ ክብርና ሉዓላዊነት የተንጸባረቀበት በመሆኑ ኢትዮጵያ አሸንፋለች ብለዋል። ከለውጡ ማግስት የተደረገው መጠነ ሰፊ የፖለቲካ ሪፎርም የፓርቲዎችን እንግልትና ስደት በማስቀረት ጤናማ የፖለቲካ የፉክክር ምኅዳር መፈጠሩን ገልጸዋል። የሕግና ፖሊሲ ማሻሻያም በስድስተኛውና በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲዎችን ተሳትፎ በማሳደግ አዲስ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ እንዲወለድ ማድረጉን አስረድተዋል። ይህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የሥልጣን ምንጭ ከህዝብ የሚሰጥ ድምፅ መሆኑን በመገንዘብ በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ የሚጠበቅባቸውን ገንቢ ሚና የሚወጡበትን ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም የፖለቲካ ፓርቲዎች የውስጥና የውጭ ጫናን በመቋቋም ጭምር ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ አሻራቸውን ላሳረፉ አካላት ምሥጋና አቅርበዋል። የለውጡ መንግሥት በሀገራዊ የጋራ ጥቅሞች ላይ ከፉክክር ይልቅ በትብብር ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ሥርዓት በመዘርጋት በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በብሔራዊ ጥቅም ላይ ወጥ የሆነ አቋም እንዲይዙ አድርጓቸዋል ብለዋል። ይሄ ትልቅ የዴሞክራሲ ትሩፋት መሆኑን በማንሳት፤ ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው በፓርቲዎች መካከል መተማመን በመፍጠር የኢትዮጵያን መዳከም የሚሹ ኃይሎችና ታሪካዊ ጠላቶችን ማሳፈሩን ገልጸዋል።
ፈረንሳይ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች
Jun 25, 2026 128
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ ፈረንሳይ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፋለች። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ይፋዊ ውጤት ማስታወቁን ተከትሎ፣ ፈረንሳይ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቷን አስተላልፋለች። ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናትና ለምርጫው ሂደት መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላትም ዕውቅና የሰጠች ሲሆን በምርጫው ሂደት ተሳትፎ ለነበራቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ታዛቢዎች ምስጋና አቅርባለች። ፈረንሳይ ከምንም በላይ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ከፍተኛ ሚና ለተወጣው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ስትል መልዕክቷን አስተላልፋለች።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻሻሉ ረቂቅ አዋጆች መርምሮ በሙሉ ድምፅ አጸደቀ
Jun 25, 2026 123
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነፃነት አዋጅ እና የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የማሻሻያ ረቂቅ አዋጆችን አጽድቋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፓርት አዳምጧል። እንዲሁም የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመረጃ ነፃነት አዋጅን አስመልክቶ ያቀረበውን የሪፓርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አፅድቋል። የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ በወቅቱ፤ ረቂቅ አዋጁ የዜጎችን መረጃ የመጠየቅና ማግኘት መብት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። አዋጁ አለም አቀፍ መብቶችን በመጠበቅ ፈጣን ቀልጣፋና ወቅቱ የጠበቀ መረጃ ፍሰት የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም የሀገራችንን ብሄራዊ ደህንነት በሚያረጋግጥ መልኩ የተዘጋጀ በመሆኑ ምክር ቤቱ እንዲያጸድቀው ጠይቀዋል። ይህን ተከትሎም አዋጅ ቁጥር 1427/2018 ሆኖ ተሻሽሎ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል። በሌላ በኩል ምክር ቤቱ የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን አፅድቋል። የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እፀገነት መንግስቱ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ የኢትዮጵያን የፍትህ ሥርዓት በማሻሻል ረገድ እጅግ የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል። የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለማቋቋም፣ የፍርድ ቤቶችን የሥራ ተደራሽነት ይበልጥ ለማስፋት እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በዚህም አዋጅ ቁጥር 18/2018 ሆኖ ተሻሽሎ በሙሉ ድምፅ ጸድቋል።
በምርጫው ካሸነፈው ብልፅግና ፓርቲ ጋር በብሔራዊ ጥቅም እና በትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በትብብር ለመሥራት ቁርጠኛ ነን -የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jun 25, 2026 157
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- በምርጫው ካሸነፈው ብልፅግና ፓርቲ ጋር በብሔራዊ ጥቅም እና በትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በትብብር ለመሥራት ቁርጠኛ መሆናቸውን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው 7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ የተሳተፈበትና በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፉክክር መድረክ የሆነበት ታሪካዊ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል። በምርጫው ሂደት ላይ የህዝቡም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ብስለትና አስተዋይነት በግልጽ የታየበት በመሆኑ፣ ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ሊጠናቀቅ ችሏል። የምርጫውን ውጤት ተከትሎም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለአሸናፊው ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት እያስተላለፉ የሚገኙ ሲሆን፣ በቀጣይም ለሀገር ልማትና አንድነት በጋራ ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት በመግለጽ ላይ ናቸው። የኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እንዳስታወቁት፤ የምርጫ ሂደቱ ጠንካራ የህዝብ ተሳትፎ የታየበት መሆኑን ህዝቡ ለምርጫው ውጤታማነት ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ያሳየው ተሳትፎ እጅግ አስደናቂ ነበር፡፡ በምርጫ ወቅትም በነቂስ በመውጣት በሰለጠነ አግባብ በሰላማዊ ሁኔታ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመንግስት ስልጣን መያዝ የሚገባ መሆኑን ትልቅ ትምህርት መስጠት መቻላቸውን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የሴቶች መምሪያ ሃላፊና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሴቶች ክንፍ ስራ አስፈጻሚ እመቤት ቢራራ እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች በነቂስ ወጥተው የመረጡበት ታሪካዊ ሂደት ነው። ሴቶችም ከማለዳው ጀምሮ በከፍተኛ ተነሳሽነት በምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት መሳተፋቸውን ጠቁመው፤ ሴቶች በከፍተኛ ቁጥር በምርጫው መሳተፋቸውን አንስተዋል፡፡ የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ነጻነት ጣሰው በበኩላቸው፤ በጠቅላላ ምርጫው የታየው ሰፊ የሕዝብ ተሳትፎ ለዴሞክራሲ ስርዓት መጠናከርና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ፅኑ መሰረት የጣለ መሆኑን አስታውቀዋል። መንግስት አካታችነት ላይ በትኩረት በመስራቱ በርካታ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በሂደቱ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ የተደረገው ጥረት ለምርጫው ስኬታማነትና ተአማኒነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል ብለዋል። በቀጣይ ፓርቲው ህዝባዊ አደራን ተቀብሎ መንግስት ለመሆን ከበቃው ብልፅግና ፓርቲ ጋር በልማት እና በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የሴቶች መምሪያ ሃላፊና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሴቶች ክንፍ ስራ አስፈጻሚ እመቤት ቢራራ ኢዜማ በብሔራዊ ጥቅም በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከአሸናፊው ብልፅግና ፓርቲ ጋር በቅርበትና በትብብር ለመስራት ሙሉ ቁርጠኝነት እንዳላቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የሁላችንም ተወዳዳሪዎች የጋራ መኖሪያ በመሆኗ ለላቀ እድገቷ በጋራ መስራት ይገባናል ያሉት ደግሞ የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ነጻነት ጣሰው ናቸው፡፡
ኢትዮጵያን በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም ያልደከሙ ልቦች
Jun 25, 2026 256
ምድረ ቀደምቷ ሀገር ኢትዮጵያ በሀገርነት ቀድማ ብትገኝም ከስልጣኔ ፈር ወደ ኋላ መቅረቷ ይወሳል። ለዘመናት ሲንከባለሉ የቆዩ ችግሮች ደግሞ በስልጣኔ ጎዳና ወደፊት እንዳትራመድ እግር ከወርች አስረዋት የቆዩ ጉዳዮች መሆናቸውም ይታወቃል ። ለዘመን ዘለል የቅራኔና አለመግባባት መንስኤ የሆኑ ችግሮችን በሰለጠነ ሀገራዊ የምክክር ሂደት በዘላቂነት ዕልባት ሰጥቶ ኢትዮጵያ የነገ መሻቷን ዕውን ታደርግ ዘንድ ታዲያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ወደስራ ከገባ ጥቂት ዓመታት አልፈዋል። ሂደቱንና ኮሚሽኑን ለመምራት ደግሞ ዕድሜ እና ዕውቀት ጠገብ ኮሚሽነሮች ተሹመው ያለመታከት ሲሰሩ ቆይተዋል። ኮሚሽነሮችም ባለፉት ዓመታት በነበሩ የምክክር ሂደት የተጠቃለሉ ስምንት አጀንዳዎችን ትናንት ማምሻውን ይፋ አድርገዋል። ኢትዮጵያን በጽኑ መሰረት ላይ የማቆም ሂደትን እንዲመሩ የተሰጣቸውን ክብርና ከባድ ሀላፊነት የተረዱት እነዚህ ኮሚሽነሮች ያለምንም ድካም መድረክ ላይ ተሰድረው ቆመው አጀንዳዎቹን ይፋ ያደረጉበት አጋጣሚ ደግሞ በበርካቶች ዘንድ ከበሬታ አስችሯቸዋል። አብዛኛዎቹ ኮሚሽነሮች ሀገራቸውን በተለያዩ ሃላፊነቶች ዕድሜ ዘመናቸውን ያገለገሉት አንጋፋ ኢትዮጵያዊያን ናቸው። የእነዚህ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ድርጊት ዛሬም በማመሻ ዕድሜያቸው ሀገራቸውን ለማገልገል ያላቸውን ውስጣዊ ጽኑ መሻት ያረጋገጠና ለኢትዮጰያ ሕልውና የሚበጅ ብሔራዊ መግባባት የመፍጠር ትጋትና ቁርጥኝነትን የገለጠ አጋጣሚ ነው። ሀገር በጽኑ መሰረት ላይ የምትቆመው ሁሉም ዜጋ ዕውቀት፣ ጥበብና ሃላፊነት ሲያዋጣ እንደሆነ ኮሚሽነሮቹ ሁነኛ ማሳያ ናቸው። የኢትዮጵያ የዘመን ዕንቆቅልሽ የሚፈታው፣ የሀገረ መንግስት ግንባታዋ የሚሳለጠው፣ በስልጣኔ ጎዳናዋ ላይ የተጋረጡ ጉድፎችና እንከኖች የሚነጹት በስልጡን ሀገራዊ ውይይትና ምክክር ብቻ መሆኑን ልባቸው የነገራቸው፣ ዕውቀትና ዕድሜ ያስተማራቸው አርዓያዎችም ናቸው፡፡ Ethiopian News Agency #ምክክር #ኢዜአ
ለህዝቡ የገባነውን ቃል በተግባር በመፈጸም ታሪካዊ ግዴታችንን እንወጣለን - አቶ ፍቃዱ ተሰማ
Jun 25, 2026 233
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- ብልፅግና ፓርቲ ለህዝቡ የገባውን ቃል በተግባር በመፈጸም ታሪካዊ ግዴታውን በብቃት እንደሚወጣ የፓርቲው ዋና ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትርና የፌደራል ተቋማት አደረጃጀት አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች የመረጡት ሰላም፣ ዴሞክራሲ፣ ልማትና መልካም አስተዳደርን መሆኑንም ተናግረዋል። የፌዴራል ተቋማት የብልፅግና ፓርቲ የፓርቲው አባል የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የሰባተኛው የጠቅላላ ምርጫ የማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው። አቶ ፍቃዱ ተሰማ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር፤ የፌደራል ተቋማት አመራሮች ለሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫው ስኬት አይተኬ ሚና መወጣታቸውን ገልጸዋል። አመራሮቹ ምርጫውን በማስተባበር፣ በሱፐርቪዥን፣ በምርጫ ክርክሮች በንቃት በመሳተፍና ከሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ጋር ጠንካራ ግንኙነት በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን ተናግረዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ነፃ ሆኖ በብልፅግና ፓርቲ አሸናፊነት እንዲጠናቀቅ በማድረግም ታሪካዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደተቻለ አብራርተዋል። የምርጫው ስኬት ብልፅግና ፓርቲ ጠንካራ መዋቅር እንዳለው በተግባር የተረጋገጠበት ታሪካዊ ሁነት መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በስኬት በመምራት የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ተቋማት ጥንካሬ በተግባር ማሳየቱንም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በመልካም የፉክክርና ትብብር መንፈስ በመንቀሳቀስ፣ የሲቪክ ማህበራትና የመገናኛ ብዙኅን ሚዛናዊ ዘገባዎችን በማቅረብ ለምርጫው ስኬት ገንቢ ሚና መወጣታቸውን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንም ገለልተኛ ሆኖ ምርጫውን በመታዘብ ታሪካዊ ኃላፊነቱን መወጣቱን አብራርተዋል። ህዝቡም በምርጫ ዕለት ከሌሊቱ አሥር ሰዓት በመነሳት እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በጽናት ድምፅ መስጠቱ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዳረጋገጠ አስታውሰዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች የመረጡት ሰላም፣ ዴሞክራሲ፣ ልማትና መልካም አስተዳደርን እንደሆነም አስረድተዋል። በዚህም ብልፅግና ፓርቲ በድህረ-ምርጫ ለህዝቡ የገባውን ቃል በተግባር በመፈጸም ታሪካዊ ግዴታውን በብቃት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። የፌደራል ተቋማት አመራሮችም ፓርቲው የገባውን ቃል በብቃት በመፈጸም ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በትጋት መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡት ስምንቱ አጀንዳዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ የተቀዱ ናቸው - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jun 25, 2026 534
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡት ስምንቱ አጀንዳዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ ድምፅ፣ ቅሬታ፣ ፍላጎት፣ ተስፋና ስጋት የተቀዱ ናቸው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታወቁ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ላለፉት አራት ዓመታት በመላው ኢትዮጵያና ከሀገር ውጭ ጭምር በመንቀሳቀስ፣ ከሁለት መቶ ሺህ በላይ ዜጎችን በማማከርና በማወያየት የሰበሰባቸውንና ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ግብአት የሚሆኑ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ዘላቂ ሰላም፣ ሀገራዊ መግባባት እና የጋራ እጣ ፈንታን በጋራ መበየን እጅግ አስፈላጊ በሆነበት ታሪካዊ መንገድ ላይ ትገኛለች። ኮሚሽኑ ይህንን ታሪካዊ ጥሪ ለመመለስ በማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 በተሰጠው ስልጣን መሰረት፣ የህዝብን ቀጥተኛ ተሳትፎ ያረጋገጠና "ከታች ወደ ላይ" የሚለውን ስልት የተከተለ አካታችና ሁሉን አቀፍ ስራ ማከናወኑን አስታውቀዋል። ይፋ የተደረጉት ስምንት ሀገራዊ አጀንዳዎች ሙሉ በሙሉ ከራሱ ከኢትዮጵያ ህዝብ ድምፅ፣ ቅሬታ፣ ፍላጎት፣ ተስፋና ስጋት የተቀዱ መሆናቸውን አብራርተዋል። ሂደቱ ተአማኒና ሁሉንም ማህበረሰብ ያካተተ እንዲሆን ለማድረግም በሁሉም ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ሰፊ የህዝብ ምክክር መካሄዱን ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የፌዴራል ተቋማት አመለካከታቸውን ያበረከቱ ሲሆን፤ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላትም በሂደቱ ላይ ትርጉም ያለው ተሳትፎ በማድረግ ድምፃቸው እንዲካተት ተደርጓል ብለዋል። ኮሚሽኑ ለግለሰቦች፣ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ለፖለቲካ ፓርቲዎች በሩን ክፍት በማድረግ ግብዓቶችን መሰብሰቡን ጠቅሰዋል፡፡ ይህም የህዝብን ተሳትፎ ማሳደግ ብቻ ሳይሆን፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ለሀገራዊ ችግሮች መፍትሄ ማምጣት እንደሚችል መልዕክት ያስተላለፈ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በጥንቃቄ የታዩት እነዚህ ግብዓቶች በኢሜል፣ በፖስታ፣ በስልክ፣ በማህበራዊ ሚዲያና በአካል በመገኘት የተሰበሰቡ ሲሆን፣ ሂደቱን ይበልጥ ለማጠናከር የአካዳሚክና የፖሊሲ ጥናት ግኝቶችም በጥልቀት ጥቅም ላይ ውለዋል ነው ያሉት። የአጀንዳዎቹ ልየታና ቀረጻ ሂደቱ ግልጽና ስርዓቱን የተከተለ እንደነበር የገለጹት ፕሮፌሰር መስፍን፣ ሂደቱ ሶስት ዋና ዋና ደረጃዎችን ያለፈ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የመጀመሪያ ደረጃ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የአጀንዳ ግብዓቶችን የመሰብሰብ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የአጀንዳ ቀረጻ የአሰራር ስርዓት በመቅረጽ፣ ጉዳዮችን በየፈርጁ የማደራጀት፣ የማጠናከርና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የመለየት ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል፡፡ በሶስተኛ ደረጃ እጅግ መሰረታዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን መስፈርቶች መሰረት በማድረግ በኮሚሽኑ ምክር ቤት ሰፊ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን፤ በሀገር ደረጃ ምክክር የሚደረግባቸውና የማይደረግባቸው ተለይተው መጣራታቸውንም ጠቁመዋል። ኮሚሽኑ ሀገራዊ ተብለው በተለዩት አጀንዳዎች ዙሪያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማድረግ፣ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የሚቀርቡት ስምንት አጀንዳዎችን ለህዝብ ይፋ አድርገዋል፡፡ ለዋናው ሀገራዊ ምክክሩ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ 1. የሀገር ግንባታ 2. የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት 3. የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ 4. የሃይማኖት ጉዳዮች 5. የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች 6. ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች 7. ሙስናና መልካም አስተዳደር 8. ሰላም ግንባታ ናቸው። እነዚህ አጀንዳዎች በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ከውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን (ዲያስፖራ) እስከ ሲቪል ማህበረሰብ፣ እንዲሁም ከፌደራል ተቋማት እስከ ክልል መንግስታት ድረስ በተካሄዱ ሰፊ፣ አካታችና ግልጽ የሆኑ ሂደቶች የተዘጋጁ መሆናቸውን ፕሮፌሰር መስፍን አብራርተዋል። የምክክሩ ስኬት የሁሉንም ዜጋ በጎ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ፣ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በሂደቱ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ በኮሚሽኑ ስም ጥሪ አቅርበዋል። ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በተለይም ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ተቋማት የሚከተሉትን የተናጠል የስራ መመሪያና ጥሪ አስተላልፈዋል፦ ከ130 ሚሊዮን በላይ የሚሆነውን የሀገሪቱን ህዝብ ወክለው በሂደቱ ላይ የሚሳተፉ የህዝብ ወኪሎች እነዚህን የተዘጋጁ አጀንዳዎች በትልቅ ትኩረት እንዲያጠኑና እንዲመረምሩ አሳስበዋል። ወኪሎቹ በሚቀጥለው የምክክር ሂደት ውስጥ የወከሉትን ህዝብ እውነተኛ ሀሳብ በግልጽ ማሰማትና ለሀገራዊ መግባባት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ማናቸውም የፖለቲካ ፓርቲዎች ከራሳቸው የፓርቲ ጥቅም በላቀ ሁኔታ በመቆም፣ ለሀገራዊ መግባባቱ መሳካት የድርሻቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል። የሲቪል ማህበረሰብ በህብረተሰቡ ውስጥ ያሉና ድምፃቸው በቀላሉ የማይሰማ የተገለሉ ቡድኖችን ድምፅ በትጋት እንዲያሰሙ ጥሪ አቅርበዋል። የሃይማኖት ተቋማት የኢትዮጵያን ነባር የምክክርና የእርቅ ባህል በጽኑ እንዲደግፉና እንዲያጠናክሩ አሳስበዋል። ወጣቶችና ሴቶችም ለምክክሩ ትኩረት በመስጠት በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ መገናኛ ብዙሃን የቀረቡት አጀንዳዎች ሀገሪቱን ወደ ልማትና ሰላም የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን በሚያሳይ መልኩ መረጃዎችን ለህዝብ ማድረስ እንዳለባቸው ፕሮፌሰር መስፍን አጽንኦት ሰጥተው አሳስበዋል።
ለዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች
Jun 24, 2026 1391
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሚጀመረው ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። ለዋናው ሀገራዊ ምክክሩ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች 1- የሀገር ግንባታ 2 -የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት 3 -የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬደዋ 4- የሃይማኖት ጉዳዮች 5- የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች 6 -ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች 7 -ሙስናና መልካም አስተዳደር 8 -ሰላም ግንባታ
ፖለቲካ
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ባህል ወደ አዲስ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ
Jun 25, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ባህል ወደ አዲስ ምዕራፍ እንዲሸጋገር እየተደረገ መሆኑን በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ 42 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በርካታ ሚሊዮን ዜጎች በድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ የተሳተፉበት ታሪካዊ ምርጫ ሆኖ ተጠናቋል። የአፍሪካ ህብረት፣ የኢጋድ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና በርካታ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችም የምርጫውን ሂደት ነጻ፣ ፍትሐዊነትና ገለልተኝነት እማኝነታቸውን በመስጠት አረጋግጠዋል። በምርጫው ዕለትም ዜጎች ከማለዳው 10 ሰዓት እስከ እኩለ ሌሊት ድርስ በመሰለፍ ጭምር ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት አስመስክረዋል። በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲዎችና የፖሊሲ ብቻ ሳይሆን የሥርዓት ምርጫ ጭምር ነው። የዴሞክራሲ ተቋማትና ሉዓላዊ የሥልጣን ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃና ገለልተኛነታቸውን በተግባር ያረጋገጡበት ምርጫ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን እውነተኛ ዴሞክራሲ መሻታቸውን ለወዳጅም ለጠላትም ያሳዩበት መሆኑን ገልጸው፤ ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ የተዋንያን ቅንጅት መንጸባረቁንም አድንቀዋል። ምርጫው ከፖለቲካ ፓርቲዎች ውድድር ባለፈ ብሔራዊ ክብርና ሉዓላዊነት የተንጸባረቀበት በመሆኑ ኢትዮጵያ አሸንፋለች ብለዋል። ከለውጡ ማግስት የተደረገው መጠነ ሰፊ የፖለቲካ ሪፎርም የፓርቲዎችን እንግልትና ስደት በማስቀረት ጤናማ የፖለቲካ የፉክክር ምኅዳር መፈጠሩን ገልጸዋል። የሕግና ፖሊሲ ማሻሻያም በስድስተኛውና በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲዎችን ተሳትፎ በማሳደግ አዲስ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ እንዲወለድ ማድረጉን አስረድተዋል። ይህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የሥልጣን ምንጭ ከህዝብ የሚሰጥ ድምፅ መሆኑን በመገንዘብ በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ የሚጠበቅባቸውን ገንቢ ሚና የሚወጡበትን ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም የፖለቲካ ፓርቲዎች የውስጥና የውጭ ጫናን በመቋቋም ጭምር ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ አሻራቸውን ላሳረፉ አካላት ምሥጋና አቅርበዋል። የለውጡ መንግሥት በሀገራዊ የጋራ ጥቅሞች ላይ ከፉክክር ይልቅ በትብብር ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ሥርዓት በመዘርጋት በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በብሔራዊ ጥቅም ላይ ወጥ የሆነ አቋም እንዲይዙ አድርጓቸዋል ብለዋል። ይሄ ትልቅ የዴሞክራሲ ትሩፋት መሆኑን በማንሳት፤ ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው በፓርቲዎች መካከል መተማመን በመፍጠር የኢትዮጵያን መዳከም የሚሹ ኃይሎችና ታሪካዊ ጠላቶችን ማሳፈሩን ገልጸዋል።
ፈረንሳይ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች
Jun 25, 2026 128
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ ፈረንሳይ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፋለች። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ይፋዊ ውጤት ማስታወቁን ተከትሎ፣ ፈረንሳይ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቷን አስተላልፋለች። ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናትና ለምርጫው ሂደት መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላትም ዕውቅና የሰጠች ሲሆን በምርጫው ሂደት ተሳትፎ ለነበራቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ታዛቢዎች ምስጋና አቅርባለች። ፈረንሳይ ከምንም በላይ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ከፍተኛ ሚና ለተወጣው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ስትል መልዕክቷን አስተላልፋለች።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻሻሉ ረቂቅ አዋጆች መርምሮ በሙሉ ድምፅ አጸደቀ
Jun 25, 2026 123
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነፃነት አዋጅ እና የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የማሻሻያ ረቂቅ አዋጆችን አጽድቋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፓርት አዳምጧል። እንዲሁም የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመረጃ ነፃነት አዋጅን አስመልክቶ ያቀረበውን የሪፓርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አፅድቋል። የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ በወቅቱ፤ ረቂቅ አዋጁ የዜጎችን መረጃ የመጠየቅና ማግኘት መብት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። አዋጁ አለም አቀፍ መብቶችን በመጠበቅ ፈጣን ቀልጣፋና ወቅቱ የጠበቀ መረጃ ፍሰት የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም የሀገራችንን ብሄራዊ ደህንነት በሚያረጋግጥ መልኩ የተዘጋጀ በመሆኑ ምክር ቤቱ እንዲያጸድቀው ጠይቀዋል። ይህን ተከትሎም አዋጅ ቁጥር 1427/2018 ሆኖ ተሻሽሎ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል። በሌላ በኩል ምክር ቤቱ የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን አፅድቋል። የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እፀገነት መንግስቱ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ የኢትዮጵያን የፍትህ ሥርዓት በማሻሻል ረገድ እጅግ የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል። የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለማቋቋም፣ የፍርድ ቤቶችን የሥራ ተደራሽነት ይበልጥ ለማስፋት እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በዚህም አዋጅ ቁጥር 18/2018 ሆኖ ተሻሽሎ በሙሉ ድምፅ ጸድቋል።
በምርጫው ካሸነፈው ብልፅግና ፓርቲ ጋር በብሔራዊ ጥቅም እና በትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በትብብር ለመሥራት ቁርጠኛ ነን -የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jun 25, 2026 157
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- በምርጫው ካሸነፈው ብልፅግና ፓርቲ ጋር በብሔራዊ ጥቅም እና በትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በትብብር ለመሥራት ቁርጠኛ መሆናቸውን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው 7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ የተሳተፈበትና በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፉክክር መድረክ የሆነበት ታሪካዊ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል። በምርጫው ሂደት ላይ የህዝቡም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ብስለትና አስተዋይነት በግልጽ የታየበት በመሆኑ፣ ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ሊጠናቀቅ ችሏል። የምርጫውን ውጤት ተከትሎም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለአሸናፊው ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት እያስተላለፉ የሚገኙ ሲሆን፣ በቀጣይም ለሀገር ልማትና አንድነት በጋራ ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት በመግለጽ ላይ ናቸው። የኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እንዳስታወቁት፤ የምርጫ ሂደቱ ጠንካራ የህዝብ ተሳትፎ የታየበት መሆኑን ህዝቡ ለምርጫው ውጤታማነት ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ያሳየው ተሳትፎ እጅግ አስደናቂ ነበር፡፡ በምርጫ ወቅትም በነቂስ በመውጣት በሰለጠነ አግባብ በሰላማዊ ሁኔታ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመንግስት ስልጣን መያዝ የሚገባ መሆኑን ትልቅ ትምህርት መስጠት መቻላቸውን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የሴቶች መምሪያ ሃላፊና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሴቶች ክንፍ ስራ አስፈጻሚ እመቤት ቢራራ እንዳሉት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች በነቂስ ወጥተው የመረጡበት ታሪካዊ ሂደት ነው። ሴቶችም ከማለዳው ጀምሮ በከፍተኛ ተነሳሽነት በምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት መሳተፋቸውን ጠቁመው፤ ሴቶች በከፍተኛ ቁጥር በምርጫው መሳተፋቸውን አንስተዋል፡፡ የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ነጻነት ጣሰው በበኩላቸው፤ በጠቅላላ ምርጫው የታየው ሰፊ የሕዝብ ተሳትፎ ለዴሞክራሲ ስርዓት መጠናከርና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ፅኑ መሰረት የጣለ መሆኑን አስታውቀዋል። መንግስት አካታችነት ላይ በትኩረት በመስራቱ በርካታ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በሂደቱ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ የተደረገው ጥረት ለምርጫው ስኬታማነትና ተአማኒነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል ብለዋል። በቀጣይ ፓርቲው ህዝባዊ አደራን ተቀብሎ መንግስት ለመሆን ከበቃው ብልፅግና ፓርቲ ጋር በልማት እና በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የሴቶች መምሪያ ሃላፊና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሴቶች ክንፍ ስራ አስፈጻሚ እመቤት ቢራራ ኢዜማ በብሔራዊ ጥቅም በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከአሸናፊው ብልፅግና ፓርቲ ጋር በቅርበትና በትብብር ለመስራት ሙሉ ቁርጠኝነት እንዳላቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የሁላችንም ተወዳዳሪዎች የጋራ መኖሪያ በመሆኗ ለላቀ እድገቷ በጋራ መስራት ይገባናል ያሉት ደግሞ የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ነጻነት ጣሰው ናቸው፡፡
ኢትዮጵያን በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም ያልደከሙ ልቦች
Jun 25, 2026 256
ምድረ ቀደምቷ ሀገር ኢትዮጵያ በሀገርነት ቀድማ ብትገኝም ከስልጣኔ ፈር ወደ ኋላ መቅረቷ ይወሳል። ለዘመናት ሲንከባለሉ የቆዩ ችግሮች ደግሞ በስልጣኔ ጎዳና ወደፊት እንዳትራመድ እግር ከወርች አስረዋት የቆዩ ጉዳዮች መሆናቸውም ይታወቃል ። ለዘመን ዘለል የቅራኔና አለመግባባት መንስኤ የሆኑ ችግሮችን በሰለጠነ ሀገራዊ የምክክር ሂደት በዘላቂነት ዕልባት ሰጥቶ ኢትዮጵያ የነገ መሻቷን ዕውን ታደርግ ዘንድ ታዲያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ወደስራ ከገባ ጥቂት ዓመታት አልፈዋል። ሂደቱንና ኮሚሽኑን ለመምራት ደግሞ ዕድሜ እና ዕውቀት ጠገብ ኮሚሽነሮች ተሹመው ያለመታከት ሲሰሩ ቆይተዋል። ኮሚሽነሮችም ባለፉት ዓመታት በነበሩ የምክክር ሂደት የተጠቃለሉ ስምንት አጀንዳዎችን ትናንት ማምሻውን ይፋ አድርገዋል። ኢትዮጵያን በጽኑ መሰረት ላይ የማቆም ሂደትን እንዲመሩ የተሰጣቸውን ክብርና ከባድ ሀላፊነት የተረዱት እነዚህ ኮሚሽነሮች ያለምንም ድካም መድረክ ላይ ተሰድረው ቆመው አጀንዳዎቹን ይፋ ያደረጉበት አጋጣሚ ደግሞ በበርካቶች ዘንድ ከበሬታ አስችሯቸዋል። አብዛኛዎቹ ኮሚሽነሮች ሀገራቸውን በተለያዩ ሃላፊነቶች ዕድሜ ዘመናቸውን ያገለገሉት አንጋፋ ኢትዮጵያዊያን ናቸው። የእነዚህ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ድርጊት ዛሬም በማመሻ ዕድሜያቸው ሀገራቸውን ለማገልገል ያላቸውን ውስጣዊ ጽኑ መሻት ያረጋገጠና ለኢትዮጰያ ሕልውና የሚበጅ ብሔራዊ መግባባት የመፍጠር ትጋትና ቁርጥኝነትን የገለጠ አጋጣሚ ነው። ሀገር በጽኑ መሰረት ላይ የምትቆመው ሁሉም ዜጋ ዕውቀት፣ ጥበብና ሃላፊነት ሲያዋጣ እንደሆነ ኮሚሽነሮቹ ሁነኛ ማሳያ ናቸው። የኢትዮጵያ የዘመን ዕንቆቅልሽ የሚፈታው፣ የሀገረ መንግስት ግንባታዋ የሚሳለጠው፣ በስልጣኔ ጎዳናዋ ላይ የተጋረጡ ጉድፎችና እንከኖች የሚነጹት በስልጡን ሀገራዊ ውይይትና ምክክር ብቻ መሆኑን ልባቸው የነገራቸው፣ ዕውቀትና ዕድሜ ያስተማራቸው አርዓያዎችም ናቸው፡፡ Ethiopian News Agency #ምክክር #ኢዜአ
ለህዝቡ የገባነውን ቃል በተግባር በመፈጸም ታሪካዊ ግዴታችንን እንወጣለን - አቶ ፍቃዱ ተሰማ
Jun 25, 2026 233
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- ብልፅግና ፓርቲ ለህዝቡ የገባውን ቃል በተግባር በመፈጸም ታሪካዊ ግዴታውን በብቃት እንደሚወጣ የፓርቲው ዋና ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትርና የፌደራል ተቋማት አደረጃጀት አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች የመረጡት ሰላም፣ ዴሞክራሲ፣ ልማትና መልካም አስተዳደርን መሆኑንም ተናግረዋል። የፌዴራል ተቋማት የብልፅግና ፓርቲ የፓርቲው አባል የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የሰባተኛው የጠቅላላ ምርጫ የማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው። አቶ ፍቃዱ ተሰማ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር፤ የፌደራል ተቋማት አመራሮች ለሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫው ስኬት አይተኬ ሚና መወጣታቸውን ገልጸዋል። አመራሮቹ ምርጫውን በማስተባበር፣ በሱፐርቪዥን፣ በምርጫ ክርክሮች በንቃት በመሳተፍና ከሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ጋር ጠንካራ ግንኙነት በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን ተናግረዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ነፃ ሆኖ በብልፅግና ፓርቲ አሸናፊነት እንዲጠናቀቅ በማድረግም ታሪካዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደተቻለ አብራርተዋል። የምርጫው ስኬት ብልፅግና ፓርቲ ጠንካራ መዋቅር እንዳለው በተግባር የተረጋገጠበት ታሪካዊ ሁነት መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በስኬት በመምራት የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ተቋማት ጥንካሬ በተግባር ማሳየቱንም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በመልካም የፉክክርና ትብብር መንፈስ በመንቀሳቀስ፣ የሲቪክ ማህበራትና የመገናኛ ብዙኅን ሚዛናዊ ዘገባዎችን በማቅረብ ለምርጫው ስኬት ገንቢ ሚና መወጣታቸውን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንም ገለልተኛ ሆኖ ምርጫውን በመታዘብ ታሪካዊ ኃላፊነቱን መወጣቱን አብራርተዋል። ህዝቡም በምርጫ ዕለት ከሌሊቱ አሥር ሰዓት በመነሳት እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በጽናት ድምፅ መስጠቱ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዳረጋገጠ አስታውሰዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች የመረጡት ሰላም፣ ዴሞክራሲ፣ ልማትና መልካም አስተዳደርን እንደሆነም አስረድተዋል። በዚህም ብልፅግና ፓርቲ በድህረ-ምርጫ ለህዝቡ የገባውን ቃል በተግባር በመፈጸም ታሪካዊ ግዴታውን በብቃት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። የፌደራል ተቋማት አመራሮችም ፓርቲው የገባውን ቃል በብቃት በመፈጸም ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በትጋት መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡት ስምንቱ አጀንዳዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ የተቀዱ ናቸው - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jun 25, 2026 534
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡት ስምንቱ አጀንዳዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ ድምፅ፣ ቅሬታ፣ ፍላጎት፣ ተስፋና ስጋት የተቀዱ ናቸው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታወቁ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ላለፉት አራት ዓመታት በመላው ኢትዮጵያና ከሀገር ውጭ ጭምር በመንቀሳቀስ፣ ከሁለት መቶ ሺህ በላይ ዜጎችን በማማከርና በማወያየት የሰበሰባቸውንና ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ግብአት የሚሆኑ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ዘላቂ ሰላም፣ ሀገራዊ መግባባት እና የጋራ እጣ ፈንታን በጋራ መበየን እጅግ አስፈላጊ በሆነበት ታሪካዊ መንገድ ላይ ትገኛለች። ኮሚሽኑ ይህንን ታሪካዊ ጥሪ ለመመለስ በማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 በተሰጠው ስልጣን መሰረት፣ የህዝብን ቀጥተኛ ተሳትፎ ያረጋገጠና "ከታች ወደ ላይ" የሚለውን ስልት የተከተለ አካታችና ሁሉን አቀፍ ስራ ማከናወኑን አስታውቀዋል። ይፋ የተደረጉት ስምንት ሀገራዊ አጀንዳዎች ሙሉ በሙሉ ከራሱ ከኢትዮጵያ ህዝብ ድምፅ፣ ቅሬታ፣ ፍላጎት፣ ተስፋና ስጋት የተቀዱ መሆናቸውን አብራርተዋል። ሂደቱ ተአማኒና ሁሉንም ማህበረሰብ ያካተተ እንዲሆን ለማድረግም በሁሉም ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ሰፊ የህዝብ ምክክር መካሄዱን ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የፌዴራል ተቋማት አመለካከታቸውን ያበረከቱ ሲሆን፤ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላትም በሂደቱ ላይ ትርጉም ያለው ተሳትፎ በማድረግ ድምፃቸው እንዲካተት ተደርጓል ብለዋል። ኮሚሽኑ ለግለሰቦች፣ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ለፖለቲካ ፓርቲዎች በሩን ክፍት በማድረግ ግብዓቶችን መሰብሰቡን ጠቅሰዋል፡፡ ይህም የህዝብን ተሳትፎ ማሳደግ ብቻ ሳይሆን፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ለሀገራዊ ችግሮች መፍትሄ ማምጣት እንደሚችል መልዕክት ያስተላለፈ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በጥንቃቄ የታዩት እነዚህ ግብዓቶች በኢሜል፣ በፖስታ፣ በስልክ፣ በማህበራዊ ሚዲያና በአካል በመገኘት የተሰበሰቡ ሲሆን፣ ሂደቱን ይበልጥ ለማጠናከር የአካዳሚክና የፖሊሲ ጥናት ግኝቶችም በጥልቀት ጥቅም ላይ ውለዋል ነው ያሉት። የአጀንዳዎቹ ልየታና ቀረጻ ሂደቱ ግልጽና ስርዓቱን የተከተለ እንደነበር የገለጹት ፕሮፌሰር መስፍን፣ ሂደቱ ሶስት ዋና ዋና ደረጃዎችን ያለፈ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የመጀመሪያ ደረጃ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የአጀንዳ ግብዓቶችን የመሰብሰብ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የአጀንዳ ቀረጻ የአሰራር ስርዓት በመቅረጽ፣ ጉዳዮችን በየፈርጁ የማደራጀት፣ የማጠናከርና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የመለየት ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል፡፡ በሶስተኛ ደረጃ እጅግ መሰረታዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን መስፈርቶች መሰረት በማድረግ በኮሚሽኑ ምክር ቤት ሰፊ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን፤ በሀገር ደረጃ ምክክር የሚደረግባቸውና የማይደረግባቸው ተለይተው መጣራታቸውንም ጠቁመዋል። ኮሚሽኑ ሀገራዊ ተብለው በተለዩት አጀንዳዎች ዙሪያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማድረግ፣ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የሚቀርቡት ስምንት አጀንዳዎችን ለህዝብ ይፋ አድርገዋል፡፡ ለዋናው ሀገራዊ ምክክሩ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ 1. የሀገር ግንባታ 2. የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት 3. የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ 4. የሃይማኖት ጉዳዮች 5. የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች 6. ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች 7. ሙስናና መልካም አስተዳደር 8. ሰላም ግንባታ ናቸው። እነዚህ አጀንዳዎች በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ከውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን (ዲያስፖራ) እስከ ሲቪል ማህበረሰብ፣ እንዲሁም ከፌደራል ተቋማት እስከ ክልል መንግስታት ድረስ በተካሄዱ ሰፊ፣ አካታችና ግልጽ የሆኑ ሂደቶች የተዘጋጁ መሆናቸውን ፕሮፌሰር መስፍን አብራርተዋል። የምክክሩ ስኬት የሁሉንም ዜጋ በጎ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ፣ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በሂደቱ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ በኮሚሽኑ ስም ጥሪ አቅርበዋል። ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በተለይም ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ተቋማት የሚከተሉትን የተናጠል የስራ መመሪያና ጥሪ አስተላልፈዋል፦ ከ130 ሚሊዮን በላይ የሚሆነውን የሀገሪቱን ህዝብ ወክለው በሂደቱ ላይ የሚሳተፉ የህዝብ ወኪሎች እነዚህን የተዘጋጁ አጀንዳዎች በትልቅ ትኩረት እንዲያጠኑና እንዲመረምሩ አሳስበዋል። ወኪሎቹ በሚቀጥለው የምክክር ሂደት ውስጥ የወከሉትን ህዝብ እውነተኛ ሀሳብ በግልጽ ማሰማትና ለሀገራዊ መግባባት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ማናቸውም የፖለቲካ ፓርቲዎች ከራሳቸው የፓርቲ ጥቅም በላቀ ሁኔታ በመቆም፣ ለሀገራዊ መግባባቱ መሳካት የድርሻቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል። የሲቪል ማህበረሰብ በህብረተሰቡ ውስጥ ያሉና ድምፃቸው በቀላሉ የማይሰማ የተገለሉ ቡድኖችን ድምፅ በትጋት እንዲያሰሙ ጥሪ አቅርበዋል። የሃይማኖት ተቋማት የኢትዮጵያን ነባር የምክክርና የእርቅ ባህል በጽኑ እንዲደግፉና እንዲያጠናክሩ አሳስበዋል። ወጣቶችና ሴቶችም ለምክክሩ ትኩረት በመስጠት በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ መገናኛ ብዙሃን የቀረቡት አጀንዳዎች ሀገሪቱን ወደ ልማትና ሰላም የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን በሚያሳይ መልኩ መረጃዎችን ለህዝብ ማድረስ እንዳለባቸው ፕሮፌሰር መስፍን አጽንኦት ሰጥተው አሳስበዋል።
ለዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች
Jun 24, 2026 1391
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሚጀመረው ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። ለዋናው ሀገራዊ ምክክሩ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች 1- የሀገር ግንባታ 2 -የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት 3 -የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬደዋ 4- የሃይማኖት ጉዳዮች 5- የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች 6 -ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች 7 -ሙስናና መልካም አስተዳደር 8 -ሰላም ግንባታ
ማህበራዊ
በትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ላይ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
Jun 25, 2026 41
ድሬዳዋ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ የትምህርትን ጥራትና ፍትሃዊ ተደራሽነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ አበረታች ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ። በድሬዳዋ አስተዳደር ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ስምንት የቅድመ መደበኛ፣ የሞዴልና የአዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ዛሬ ተጀምሯል። በአስተዳደሩ በ18 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፉትን ትምህርት ቤቶች ግንባታ ያስጀመሩት የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልዪ ናቸው። ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ በወቅቱ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በትምህርት ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙት ውጤታማ ተግባራት የትምህርት ፍትሃዊ ተደራሽነትና ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ውጤት እያሳዩ ናቸው። በተለይም በቅድመ መደበኛ ትምህርት፣ በትምህርት ቤቶች ምገባ እና በሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ላይ የተከናወኑ ተግባራት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት በተግባር ማረጋገጥ ማስቻላቸውን አንስተዋል። ከለውጡ በፊት በመላው ሀገሪቱ 4ሺህ 100 የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች እንደነበሩ አስታውሰው ከለውጡ በኃላ በገጠርና በከተማ 34 ሺህ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው ህፃናት ትምህርትን በጥራት እንዲማሩ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል። ዛሬ በድሬዳዋ የተጀመሩት የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በሀገሪቱ 726 ወረዳዎች ተጨማሪ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት በመጪው የትምህርት ዘመን አገልግሎት እንዲጀምሩ ይደረጋል ብለዋል። እንደ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ገለፃ ስምንት ሚሊዮን ህፃናትን ተጠቃሚ ያደረገው የትምህርት ቤት ምገባ ሀገራዊ መርሃ ግብርም ህፃናት ከትምህርት ገበታ እንዳይለዩና ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ አስችሏል። ዛሬ በድሬዳዋ በ606 ሚሊዮን ብር ግንባታው የተጀመረውና በአንድ ዓመት የሚጠናቀቀው የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትም የትምህርት ጥራትን የማረጋገጥ ጉዞ የሚያጠናክር ይሆናል ብለዋል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር በበኩላቸው፤ የትምህርት ሚኒስቴር በድሬዳዋ ዛሬ መገንባት የጀመራቸው ትምህርት ቤቶች የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊ ተደራሽነትን ይበልጥ ለማሳደግ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ገልጸዋል። ፕሮጀክቶቹን በባለቤትነት በመከታተልና በመደገፍ በተያዘላቸው ጊዜ፣ በጀትና ጥራት እንዲጠናቀቁ አስተዳደሩ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አስታውቀዋል ። ዘመናዊና ሞዴል ፕሮጀክቶቹ በድሬዳዋ የትምህርት ጥራትን እና ተሳትፎን ለማረጋገጥ የተጀመሩትን ስራዎች በላቀ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚያስችሉ የተናገሩት ደግሞ የአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልዪ ናቸው። በትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራው ቡድን ከግንባታ ማስጀመር ጎን ለጎን የድሬዳዋን የትምህርት ቤቶች ምገባ ማብሰያ ማዕከልና ለምገባው መርሃግብር የተዘጋጀውን 18 ሄክታር የፍራፍሬና የአትክልት ማልሚያ ስፍራን ተመልክተዋል።
ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የቀሰሙትን እውቀት በተሟላ ስነ-ምግባርና ስብዕና ተግባር ላይ ማዋል ይጠበቅባቸዋል
Jun 25, 2026 76
ነቀምቴ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ ተመራቂዎች የቀሰሙትን እውቀት በተሟላ ስነ-ምግባርና ስብዕና ተግባር ላይ ሊያውሉት ይገባል ሲሉ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ተስፋዬ ለማ (ዶ/ር) አመለከቱ። የወለጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 920 ተማሪዎች አስመርቋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ተስፋዬ ለማ (ዶ/ር) በምረቃው ወቅት እንደተናገሩት፤ ዩኒቨርሲቲው የተሳካ የመማር ማስተማር ስራ እያከናወነ ይገኛል። የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ የሥራ ገበያው የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው የተቀበላቸውን ተማሪዎች እውቀትና ክህሎት አስታጥቆ እያስመረቀ መሆኑን ጠቅሰው፤ ተመራቂዎችም የቀሰሙትን እውቀት በተሟላ ስነ-ምግባርና ስብዕና ሊተገብሩት እንደሚገባ አሳስበዋል። በዩኒቨርሲቲው በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የአካዳሚክ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት መልካ ሂካ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በነቀምቴ፣ ጊምቢ እና ሻምቡ ካምፓሶች ትምህርታቸውን የተከታተሉ 920 ተማሪዎችን ማስመረቁን ገልጸዋል። ከተመራቂዎቹ መካከልም የመጀመሪያ ዲግሪ 674፣ ሁለተኛ ዲግሪ 218፣ ሶስተኛ ዲግሪ 8 እና በሕክምና ስፔሻሊቲ 20 ተማሪዎችን ማስመረቁን ተናግረዋል። ተመራቂዎች በተለይም የሥራ ጠባቂነትን አስወግደው ሥራ ፈጣሪ በመሆን ከራሳቸው አልፈው ለሕዝብና ለሀገር ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። ተመራቂ ተማሪዎች በበኩላቸው በቀሰሙት እውቀት ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን በቅንነት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከዩኒቨርሲቲው በፋርማሲ ትምህርት ክፍል 3 ነጥብ 98 በማስመዝገብ የማዕረግ ተመራቂ የሆነው ዱሬሳ ደንቦባ፤ በተማረበት የሙያ መስክ ሀገሩን ለማገልገል ቁርጠኛ መሆኑን ተናግሯል። በተለይም ዘርፉን ለማዘመን የሚያስችሉ በጥናትና ምርምር የታገዙ አዳዲስ ሥራዎችን ለመስራት መዘጋጀቱንም ገልጿል። የሕግ ትምህርት ክፍል ተመራቂ ገለታ ጋዲሳ በበኩሉ በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ያገኘውን እውቀት በመጠቀም በፍትህ ዘርፉ ላይ የራሱን አሻራ ለማሳረፍ መዘጋጀቱን ጠቅሷል።
የወጣቶችን ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት በበጎ ሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ ማፍራት የሚያስችል ምኅዳር ፈጥረዋል
Jun 25, 2026 211
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት በበጎ ሥነ-ምግባር የታነጸ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ማፍራት የሚያስችል ምኅዳር መፍጠራቸውን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በመልካም ስብዕና የተቀረጸ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለማፍራት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት ይገኛል። ሀገር አቀፍ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶችም ከተሞችን ከማስዋብ ባሻገር ወጣቶችና ሕፃናት በአካልና በአዕምሮ የሚቀረጹበትን ምቹ የሰብዕና መገንቢያ ማዕከላት እንዲገነቡ ዕድልን ፈጥረዋል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሙና አሕመድ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የመደመር መንግሥት ለወጣቶችና ሕፃናት ስብዕና ግንባታ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው። ለዚህም በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወጣቶች ፖሊሲ በማሻሻል፣ የወጣቶችና ሕፃናትን ስብዕና ግንባታ ማሳደግ በሚያስችል መልኩ እየተሰራበት መሆኑን ገልጸዋል። የወጣቶች ስብዕና ልማት ስትራቴጂን በመቅረጽ ጭምር ለሀገር ግንባታ መሰረት የሚሆን ትውልድ ለማፍራት በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ከተሞች የኮሪደር ልማት የፈጠረው የስብዕና መገንቢያ ማዕከላት ግንባታም ለበርካታ ወጣቶችና ሕፃናት አስቻይ ምህዳር መፍጠሩን አስረድተዋል። በተለይም ለሕፃናትና ታዳጊዎች የተፈጠሩት የመጫወቻና መዝናኛ ማዕከላት የመሰረተ ልማት አስቻይ ምኅዳር፣ በበጎ ሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ ለማፍራት ጉልህ ፋይዳ እያበረከቱ መሆኑን አስረድተዋል። በበጎ ስብዕና የታነጸ ትውልድ ለማፍራት ከቤተሰብ እስከ ባለድርሻ ተቋማት ጋር የሚከናወኑ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ የስብዕና መገንቢያ ማዕከላትን አቅም፣ ጥራትና ተደራሽነት የማስፋፋትና የማሻሻል ሥራም ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸዋል። የስብዕና መገንቢያ ማዕከላትንም ወደ ማህበራዊ ኢንተርፕራይዝ በማሳደግ የገቢ አቅማቸውን ለማሻሻል እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
በዘንድሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና የተሻለ ውጤት ለማምጣት የሚስያችል ዝግጅት አድርገናል- ተማሪዎች
Jun 25, 2026 173
ቦንጋ፤ ሰኔ 18 /2018 (ኢዜአ)፦ በዘንድሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና የተሻለ ውጤት ለማምጣት የሚያስችል ዝግጅት ማድረጋቸውን በቦንጋ ከተማ አስተዳደር አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተፈታኝ ተማሪዎች ገለጹ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ በበኩሉ በዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና 17 ሺህ 458 ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀመጡ አስታውቋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተማሪዎች እንደገለፁት፤ በዘንድሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና የተሻለ ውጤት ለማምጣት የሚያስችል ዝግጅት አድርገናል። በከተማው የቢሻው ወልደ ዮሐንስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎቹ ተማሪ ናታኔም ኤፍሬም እና ተማሪ ብሩክታዊት እሸቱ እንደተናገሩት በዘንድሮ ሀገር አቀፍ ፈተና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅት አድርገዋል። ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ እስከ 12ኛ ያለውን ይዘት ከመሸፈን ባለፈ ተጨማሪ የድጋፍ ትምህርቶችን በመከታተልና የፈተና ጥያቄዎችን በመስራት ራሳቸውን የማብቃትና የመለማመድ ስራ ትኩረት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ትምህርት ቤቱና መምህራን በቂ ድጋፍ እያደረጉላቸው መሆኑን የተናገሩት ተማሪዎቹ ምሽቱን ጨምሮ ቤተ-መፃሐፍት እንዲጠቀሙ በማድረግና በስነ ልቦና ብቁ እንዲሆኑ እገዛዎች እንደተደረገላቸው ነው የገለጹት። የቦንጋ መሃል ከተማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆኑት ይንገስ ካሳሁንና ጨመረ መኮንን በበኩላቸው ዓመቱን ሙሉ በጥሩ ሁኔታ ትምህርታቸውን እንደተከታተሉ እና በቂ ድጋፍ ሲደረግላቸው መቆየቱን ገልፀዋል። ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም በግላቸውም ፕሮግራም አውጥተው ሲያጠኑ መቆየታቸውን ጠቅሰው ይህም ጥሩ ወጤት ለማስመዝገብ እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል። ፈተናው በኦላይን የሚሰጥ በመሆኑ ለዚህ የሚሆን ክህሎት እንዲኖረን በተመቻቸው ኮምፒተር ልምምድ አድርገናል ያሉት ተማሪዎቹ በተረጋጋ መንፈስ ለመስራት የስነ-ልቦና ዝግጅት በማድረግ እየተጠባበቁ መሆናቸውን አብራርተዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ገነሜ (ዶ/ር) በክልሉ 17 ሺህ 458 ተማሪዎች ሀገር አቀፍ ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል። ከነዚህም ውስጥ 9 ሺህ 602ቱ በኦላይን (በበይነ መረብ) ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ተናግረዋል። ተማሪዎቹ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በተቃራኒ ፈረቃና ቅዳሜና እሁድ የድጋፍ ትምህርቶችን በመስጠት፣ የፈተና ጥያቄዎችን በማሰራት እንዲዘጋጁ መደረጉን ጠቁመዋል። የዘንድሮ ሀገር አቀፍ ፈተና በክልሉ በ18 የፈተና ማዕከላት እንደሚሰጥ ጠቅሰው ለኦላይን ፈተና ኮምፒተሮችን እና ጄኔሬተሮችን የማዘጋጀት፣ የኢንተርኔት አቅምን የማሳደግና ሌሎች በቂ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ገልፀዋል።
ኢኮኖሚ
በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ሊጠናከር ይገባል
Jun 25, 2026 18
ጋምቤላ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ መሳካት፣ የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሯን ጨምሮ የክልልና የፌደራል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ በአቦቦ ወረዳ በሩዝ ሰብል ላይ እየተካሄደ ያለውን የምርምር ሥራ ዛሬ ጎብኝተዋል። ርዕሰ መስተዳድሯ በወቅቱ እንዳሉት፤ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚቻለው የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋትና ተደራሽ ማድረግ ሲቻል ነው። ክልሉ ያለውን ሰፊ የመሬትና የውኃ ሀብት በምርምር መደገፍ ከተቻለ፣ ለአካባቢው ብቻ ሳይሆን ለሀገር የሚተርፍ የሰብል ምርት ማግኘት እንደሚቻልም ተናግረዋል። ጋምቤላ ለሁሉም የግብርና ልማት ዓይነቶች ምቹ ሥነ-ምህዳር ያላት መሆኑን የጠቀሱት ወይዘሮ ዓለሚቱ፤ በተለይም የሩዝ ሰብል አዋጭ ተብለው ከተለዩት የሰብል ዓይነቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ የሩዝ ልማትን ማዘመንና ማስፋፋት ከተቻለ ለአገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ የሚተርፍ ምርት ማግኘት እንደሚቻልም አክለዋል። ልማቱን ለመደገፍ በባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲና በቻይናው ዩናን ዩኒቨርሲቲ ቅንጅት እየተካሄደ ያለው የምርምር ሥራ የሚበረታታ መሆኑን በመግለጽ፣ ለሥራው ስኬታማነት የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር የታለመውን የግብርና ልማት ስኬታማ ማድረግ የሚቻለው አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለአርሶ አደሩና ለባለሀብቱ ተደራሽ ማድረግ ሲቻል መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በተለያዩ ተቋማት ትብብር በሩዝ ሰብል ላይ የተጀመረው የምርምር ሥራ ተስፋ ሰጪና ዘርፉን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ በበኩላቸው፤ የምርምር ሥራው እየተካሄደ ያለው ከቻይናው ዩናን ዩኒቨርሲቲ ጋር መሆኑን አስረድተዋል። የአዲሱ የሩዝ ዝርያ ልዩ ባህሪያት መካከል በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚደርስ መሆኑ እንዲሁም በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ መመረቱ እንደሆነ ገልጸዋል። በሩዝ ዝርያዎቹ ላይ እየተካሄደ ያለው የማላመድ የምርምር ሥራ በሚቀጥለው ዓመት ተጠናቆ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እንደሚሆንም ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ117 ሺህ በላይ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል- መምሪያው
Jun 25, 2026 82
ደብረ ማርቆስ ፤ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን ባለፉት 11 ወራት ከ117 ሺህ በላይ ወጣቶች የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የዞኑ ስራና ክህሎት መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ኃላፊ አቶ ፀሐይ ቦጋለ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የተቻለው የአካባቢውን ጸጋ በጥናት በመለየትና አልምቶ ለመጠቀም በተደረገ ጥረት ነው። በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ከ 131 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር የታቀደ ሲሆን ባለፉት 11 ወራት 117 ሺህ 427 የሚሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። የተፈጠረው የስራ እድል በማዕድን ልማት ፣ በኮንስትራክሽን ፣ በግብርና ፣ በአምራች ኢንዱስትሪዎችና ሌሎች መስኮች መሆኑን ነው የጠቆሙት ። በዚሁ ወቅት የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል ከ30 በመቶ በላይ የሚሆኑት በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ተከታትለው የተመረቁ መሆናቸውንም አንስተዋል። የስራ እድል ለተፈጠረላቸው ዜጎች 491 ሚሊየን ብር በላይ ብድር፣ ከ270 በላይ የመስሪያ ሼድና ኮንቴነሮች ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም በገጠርና በከተማ በግብርና ዘርፎች ስራ ለተፈጠረላቸው ዜጎች ከ15 ሺህ ሄክታር በላይ የእርሻ መሬት በመስጠት ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን አብራርተዋል። በዞኑ የባሶሊበን ወረዳ የጁቤ ከተማ ነዋሪ ወጣት ቀለምወርቅ ገነት ፤ ከሶስት ጓደኞቹ በመደራጀት ወደ ግብርና ስራ ገብቶ ተጠቃሚ መሆን መጀመሩን ነው የሚናገረው ። የተፈጠረለት የስራ እድል ከቤተሰብ ጥገኝነት በማውጣት ገቢ ለማግኝት ከማስቻሉ ባሻገር ሀብት ለማፍራት እንዳስቻለው ነው ያመለከተው። የአዋበል ወረዳ የሉማሜ ከተማ ነዋሪ ወጣት ጌትነት ይመር በበኩሉ፤በዘንድሮው ዓመት ከአምስት ጓደኞቹ ጋር በመደራጀት በኮንስትራክሽን ዘርፍ የብሉኬት ምርት ላይ መሰማራቱን ነው የሚናገረው። በመንግስት በተመቻቸላቸው የመስሪያ ቦታን ጨምሮ የ500 ሺህ ብር ብድርና ሌሎች ድጋፎች በመነሳት ወደ ስራ ተሰማርተው ገቢ ማግኝት መጀመራቸውን ነው የሚናገረው።
የጉባ ብስራቶች -የኢትዮጵያ የማከናወን ጉዞ ቀጣይነት ማሳያዎች
Jun 25, 2026 161
ኢትዮጵያ እየተገበረች ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (Homegrown Economic Reform) መዋቅራዊ ማነቆዎችን በመስበር ረገድ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፍቷል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁ በተበሰረበት ታሪካዊ ወቅት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ ያደረጓቸው "የጉባ ብስራቶች" ሀገሪቱ በኃይል፣ በኢንዱስትሪ፣ በአቪዬሽን፣ በማዕድንና በከተማ ልማት ዘርፍ የደረሰችበትን ከፍተኛ የማስፈጸም አቅም ያሳዩ ሲሆን፣ እነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" የሚለውን አገራዊ መርህ በተግባር የሚያረጋግጡ ናቸው። ለጉባ ብስራቶች ዋነኛ ምሰሶ የነበረውና ለመላው አፍሪካ ኩራት የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ፍጻሜ ማግኘቱ የሪፎርሙ ውጤታማነት ትልቁ ማሳያ ነው። የለውጡ መንግስት የፋይናንስ ማነቆዎችን በቁርጠኝነት በመፍታት እንዲሁም ዲፕሎማሲያዊ ጫናዎችን በመቋቋም ግድቡን አጠናቅቆ ሌላ ሜጋ ፕሮጀክቶችን ጀምሯል። ይህም በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ አንዱ የታሪክ እጥፋት ነው። ኢትዮጵያ የወደፊት የኃይልና የቴክኖሎጂ ፍላጎቷን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የኒውክሌር ኃይልን ለሰላማዊ አገልግሎት ለማዋል የጀመረችው ታሪካዊ ጉዞ ሌላኛው ደማቅ ብስራት ነው። በሪፎርሙ ወቅት ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር የተደረጉት ስምምነቶችና የተጀመሩት የዝግጅት ስራዎች፣ ሀገሪቱ በሕክምና፣ በግብርና እና በኃይል አማራጮች ላይ ያላትን የረጅም ጊዜ አርቆ አሳቢነትና የከፍተኛ ቴክኖሎጂ ሽግግር ቁርጠኝነት ያሳያሉ። በሌላ በኩል የኢትዮጵያን የአቪዬሽን መሪነትና የኮሜርስ የበላይነት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስቀጠል የታለመው የአዲሱ የቢሾፍቱ ሜጋ አየር ማረፊያ (Bishoftu International Airport) በፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል። ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ በዓመት ከ110 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን ግዙፍ የጭነት አውሮፕላኖችን ለማስተናገድ የተነደፈው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ ሀገሪቱን የአፍሪካ ዋና የትራንስፖርትና የሎጂስቲክስ መገናኛ ኮሪደር የማድረግ ስትራቴጂ አካል ነው። ከዚህ በተጨማሪ በማዕድን ዘርፍ ለዘመናት ሲጠበቅ የነበረውን አገራዊ እምቅ አቅም ወደ ጥቅም ለመቀየር በኦጋዴን ተፋሰስ የተገነባው የተፈጥሮ ጋዝ ፋብሪካ ተጠናቆ በስኬት ተመርቋል። ይህ ሜጋ ፕሮጀክት ሀገሪቱ የራሷን የሃይልና የኢንዱስትሪ ግብዓት እንድታመርት አቅም የፈጠረ ሲሆን፣ ለሀገር ውስጥ የኬሚካል ኢንዱስትሪዎች ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ የሪፎርሙ ታላቅ ስኬት ነው። የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት በዘላቂነት ለማረጋገጥና በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚገባውን ግብዓት በሀገር ውስጥ ለመተካት የግዙፍ ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በይፋ ተጀምሯል። ይህ ፕሮጀክት አርሶ አደሩን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነትና ከተደጋጋሚ የእጥረት አደጋዎች የሚታደግ ከመሆኑም በላይ፣ የሀገሪቱን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የተነደፈ ስልታዊ የሪፎርሙ አካል ነው። ኢትዮጵያ በነዳጅ አቅርቦት ላይ ያላትን የውጭ ምንዛሬ ጫና ለማቃለልና የኢነርጂ ዋስትናዋን ለማጠናከር የጀመረችው የነዳጅ ማጣሪያ ግንባታ ሌላኛው ስትራቴጂካዊ የጉባ ብስራት ነው። በከተማ ልማትና በዜጎች የኑሮ ደረጃ መሻሻል ረገድ ትልቁ አገራዊ ንቅናቄ የሆነው የ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት በከፍተኛ ፍጥነት በቴክኖሎጂ በመታገዝ ጭምር እየተተገበረ ይገኛል። ይህ ፕሮጀክት የቤት ተደራሽነትን ከማሻሻሉም በላይ ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድልና የእውቅት ሽግግር ለመፍጠር ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው። በአጠቃላይ የጉባ ብስራቶች ኢትዮጵያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጉዞ ውጤታማነትን የሚያመላክቱና ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ትውልድ ዘላቂ ብልጽግናንና የኢኮኖሚ ነፃነትን የሚያረጋግጥ ታሪካዊ መሰረት እየጣለች ለመሆኑ ህያው ምስክሮች ናቸው።
በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች 117 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል
Jun 25, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች 117 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡ ኢትዮጵያ የተለያዩ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦን በማቀነባበር ለውጭ ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሪ ገቢ ታገኛለች፡፡ የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ካላት እምቅ የእንስሳት ሀብት ተገቢውን የውጭ ምንዛሪ ገቢ እንድታገኝ የእንስሳትን ምርታማነት የሚያሳድጉ አሰራሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡ ኢንስቲትዩቱ የእንስሳት ዝርያዎችን ለማሻሻል አዳዲስ የፈሳሽ ናይትሮጅን ማምረቻ ማዕከላትን እያሰፋና ነባሮችን እያዘመነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ለውጭ ገበያ ካቀረባቸው የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች 117 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል፤ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የስድስት ሚሊዮን ዶላር ብልጫ አለው ብለዋል፡፡ ለውጭ ገበያ ከቀረቡ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች መካከል የበግና ፍየል ስጋ እንዲሁም የእርድ ተረፈ ምርቶች ቀዳሚዎች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የሥጋ ምርቶቹ በብዛት ወደ ውጭ ከተላኩባቸው ሀገራት መካከል የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ኳታር መሆናቸውን ገልጸው፤ ወደ አፍሪካ ሀገራትም ይቀርባሉ ብለዋል፡፡ በአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደብረ ብርሃን ግብርና ምርምር ማዕከል የእንስሳት ጤና እና ሥነ ተዋልዶ ተመራማሪ ዶክተር ቸኮል ደምስ፤ የእንስሳት ምርታማነትን ለማሳደግ በዘርፉ ለተሰማሩ ዜጎች የእንስሳት እርባታ ሳይንስ ላይ በቂ ግንዛቤ እንደሚሰጡ ገልጸዋል፡፡ ማዕከሉ የተሻሻሉ የበግና የዳልጋ ከብት ኮርማዎች ተገቢውን እንክብካቤ አግኝተው እንዲያድጉ ለማድረግ በምርምር የተደገፈ እገዛ ያደርጋል ብለዋል፡፡ በአርባ ምንጭ ግብርና ምርምር ማዕከል የእንስሳት ጤና ማሻሻያ ተመራማሪ ዶክተር ናሆም በላይ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት ሀብት ልማትን የሚያሳድግ ፍሬያማ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም በዘርፉ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የዘርፉ ባለሙያዎች ልምዳቸውን ለእንስሳት ሀብት ልማት ማዋል እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በመደገፍ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ እምርታ እየታየ ነው
Jun 25, 2026 181
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በመደገፍ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ረገድ ትልቅ እምርታ እየታየ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የዲጂታል አግሪካልቸር ሰርቪስ ፕሮጀክት ዲንና ተመራማሪ አቶ ተመስገን ገበየሁ ገለጹ፡፡ የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት የሆነውን የግብርና ዘርፍ በቴክኖሎጂ በመደገፍ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን አስመዝግቧል፡፡ የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የዲጂታል አግሪካልቸር ሰርቪስ ፕሮጀክት ዲንና ተመራማሪ አቶ ተመስገን ገበየሁ፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ አማካኝነት ግብርናን ለማዘመን ቴክኖሎጂ በስፋት ጥቅም ላይ መዋሉን ገልጸዋል። በዚህም አርሶ አደሮች በእጅ ስልካቸው በመጠቀም ስለ ግብዓቶች አቅርቦት፣ ዋጋ እና ጊዜ መረጃ እንዲሁም ስለ አፈር፣ ዝናብና የሰብል በሽታዎች የባለሙያ ምክር በቀላሉ እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ይህ የዲጂታል ስልት አርሶ አደሩ የገበያ ዋጋን አስቀድሞ አውቆ ምርቱን በቀጥታ እንዲያቀርብ በማገዝ ምርታማነቱንና ተጠቃሚነቱን በተግባር እንዲያረጋግጥ ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ቅርጽ ለማስያዝና ፕሮግራሞችን ለመደገፍ በከፍተኛ ሁኔታ ሲጠቀምበት መቆየቱን ተመራማሪው ጠቁመዋል። በተለይም የምክር አገልግሎትን ለማገዝ በተዘረጋው የ"8028" የስልክ መስመር ከ7 ሚሊየን በላይ አርሶ አደሮች በነጻ በመደወል የምክር አገልግሎት ማግኘታቸውን ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም 344 ከሚሆኑ የገበያ ማዕከላት በየጊዜው እየተሰበሰበና ትክክለኛነቱ እየተረጋገጠ የሚሰራጨው የገበያ መረጃ እስካሁን 2 ሚሊየን የሚሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት የሆነውን ግብርና ይበልጥ በማዘመን ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ገልጸዋል። በስትራቴጂው በከተማና በገጠር መካከል ያለውን የዲጂታል ልዩነት በማጥበብ የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ የሚሰራ ሲሆን፣ ለዚህም የዲጂታል መሰረተ-ልማትና የእውቀት ማሳደጊያ ስልጠናዎች እንደሚሰጡ ጠቁመዋል፡፡ በ2030 አርሶ አደሮችን ቀልጣፋ አገልግሎት የሚያገኙበት ደረጃ ላይ ለማድረስ እንደሚሰራ ጠቁመው፤ የቴክኖሎጂ አቅሞችን ተደራሽ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል
Jun 25, 2026 132
ደሴ፤ ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፡- መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቋማትን አገልግሎት በማዘመን ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ገለፁ። ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፣መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል። አገልግሎቱ ዘመናዊ፣ፈጣን እና ቀልጣፋ መሆኑ የተገልጋዩን እንግልት ከማስቀረቱ ባሻገር ተጠያቂነትን የሚያሰፍን መሆኑንም አስረድተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ መስኮች በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ሰፊ እድል የፈጠረ መሆኑን አንስተዋል። የወልድያ ከተማ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የቴክኖሎጅ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ምስጋናው ወርቅዬ በበኩላቸው፣ በማዕከሉ 13 የከተማ አስተዳደሩና የፌዴራል ተቋማት 102 አገልግሎቶችን እየተሰጡ ይገኛሉ ብለዋል። ተቋማቱ በቴክኖሎጂ በመታገዝ በቅንጅት አገልግሎት በመስጠታቸውም ተገልጋዩ ህብረተሰብ በአንድ ቦታ እና በአጭር ጊዜ በመስተናገዱ እርካታን እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። በማዕከሉ የሁሉ አገልግሎት ባለሙያ አቶ ጥላሁን አስቻለሁ በበኩላቸው፣ ወደ ማዕከሉ የሚመጡ ተገልጋዮች አስቀድሞ መረጃ በመስጠት በቀላሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል። አገልግሎቱን በማግኝት ላይ የነበሩት የወልድያ ከተማ ነዋሪ ያልጋ ጌታሁን እንዳሉት፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ስራ መጀመሩ ከእንግልትና ከአላስፈላጊ ወጭ አድኖናል ነው የሚሉት። ቀደም ሲል ጉዳዮቻችን ለማስፈፀም የሚኬድባቸው ቦታዎች አድካሚና ረጅም ጊዜ የሚወስዱ ከመሆኑም በላይ ለእንግልት የሚዳርጉ እንደነበርም አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት ግን በማእከሉ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንደቻሉ ነው የተናገሩት።
በኦሮሚያ ክልል ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አባወራዎች በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የሶላር ፓኔል ተሰራጭቷል
Jun 24, 2026 538
አዳማ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አባወራዎች በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የሶላር ፓኔል ስርጭት መከናወኑን የክልሉ ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ገለጸ። በቢሮው የኢነርጂ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሶሬሳ እንደገለጹት፤ በክልሉ በቤተሰብ ደረጃ የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ላይ በትኩረት እየተሠራ ነው። በዚህም ከዋናው የኃይል ቋት ርቀው የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የሶላር ፓኔል ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አባወራዎች መሰራጨታቸውን ገልጸዋል። የታዳሽ ኃይል ልማትና ተደራሽነት የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። በሌላ በኩል ከዋናው የኃይል ቋት ርቀው የሚገኙ የገጠር የጤናና የትምህርት ተቋማት የኃይል አቅርቦት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም በናፍጣ የሚሠሩ የውኃ ተቋማትን ወደ ፀሐይ ኃይል በመቀየር ኅብረተሰቡ ዘላቂ የመጠጥ ውኃ አገልግሎት እንዲያገኝ መሠራቱንም ጠቁመዋል። በተያያዘም ከ700 ሺህ በላይ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችንና ከ1 ሺህ 500 በላይ የባዮ ጋዝ በመሥራት ለመብራት አገልግሎት እንዲሁም ተረፈ ምርቱ ለተፈጥሮ ማዳበሪያ እንዲውል መደረጉን ጠቁመዋል፡፡
በቀጣዩ ዓመት በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለመስጠት ግብ ተይዟል
Jun 24, 2026 531
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በቀጣዩ ዓመት በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል አንድ ማዕከል አገልግሎት ለመስጠት ግብ መያዙን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት ከመቀነስ ባሻገር የመልካም አስተዳደር ችግሮች ትርጉም ባለው መልኩ እንዲቀነሱ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአቃቂ ቃሊቲ 10ኛውን፤ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ደግሞ 11ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን መርቀው ስራ አስጀምረዋል። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ፤የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድርን ጨምሮ የመዲናዋ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር የመንግሥት አገልግሎት ቢሮክራሲ፣ ውጣ ውረድ እና እንግልት የበዛበት እንደነበር አስታውሰዋል። የመልካም አስተዳደር ችግር ዜጎች አገልግሎት በአግባቡ እንዳያገኙ ተግዳሮት ሆኖ መቆየቱን አመልክተው፤ የመሶብ አንድ ማዕከል የዲጂታል አገልግሎት ለችግሮች ሁነኛ መፍትሔ መሆኑን ገልጸዋል። በቁርጠኝነት ከሰራን የማይለወጥ ነገር እንደሌለ በአንድ ማዕከል አገልግሎት ያመጣነው ውጤት ትልቅ ማሳያ ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፥ ብልሹ አሰራር ከመሠረቱ እየተቀረፈ ነው ብለዋል። የአገልግሎት ተደራሽነትን ይበልጥ ለማስፋት ዜጎች በተንቀሳቃሽ ስልካቸው አገልግሎት የሚያገኙበት ሂደት እንደሚጠናከርም ተናግረዋል። በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመንግሥት ከሚሰጡ አገልግሎቶች 50 የሚሆኑት ወደ አንድ ማዕከል እንዲገቡ መደረጉን ጠቅሰው፥ በቀጣዩ ዓመት ሙሉ ለሙሉ ለማስገባት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። አገልግሎት አሰጣጥ ላይ አሁንም ቀሪ ስራዎች አሉ ያሉት ከንቲባ አዳነች፥ የዜጎችን እርካታ የሚያሳድጉ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ለሕዝብ የገባነውን ቃል ወደ ተግባር እየቀየርን ብልጽግናችንን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል።
ስፖርት
ሀገራት ከፍተኛ የገንዘብ መጠን የሚያጋብሱበት የዓለም ዋንጫ ክብረ ወሰን ሽልማት
Jun 25, 2026 51
በሙሴ መለሰ 23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጣምራ አዘጋጅነት መካሄድ ጀምሯል። የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ በበርካታ ነገሮች «የመጀመሪያ» የተሰኙ አዳዲስ ነገሮችን ይዟል። ከነዚህም መካከል ለውድድሩ ተሳታፊ ሀገራት የሚበረከተው የገንዘብ ሽልማት ነው። የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ለዓለም ዋንጫው ተሳታፊ ሀገራት 871 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ሽልማት ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል። ይህም በውድድሩ የ96 ዓመታት ታሪክ ከፍተኛ የሚባለው ነው። የፊፋ ምክር ቤቱ እ.አ.አ ዲሴምበር 2025 በኳታር ዶሃ ባካሄደው ስብሰባ፤ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ለሚሳተፉ አገራት የሚከፋፈል የ727 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ታሪካዊ በጀት አጽድቆ ነበር። ይህ መጀመሪያ ላይ የጸደቀው የገንዘብ መጠን፣ በኳታር አስተናጋጅነት ከተካሄደው የ2022 የዓለም ዋንጫ ጋር ሲነጻጸር የ50 በመቶ ብልጫ ያለው እንደነበር ተገልጿል። በዚሁ የኳታር ስብሰባ ላይ በጸደቀው ስሌት መሠረት፣ የውድድሩ ሻምፒዮን (ባለድል) 50 ሚሊዮን ዶላር ሲያገኝ፣ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ የሚያጠናቅቀው ቡድን 33 ሚሊዮን ዶላር፣ ሦስተኛው 29 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም አራተኛ ደረጃን የሚያገኘው 27 ሚሊዮን ዶላር ተመድቦለታል። በተመሳሳይ ከ5ኛ እስከ 8ኛ ደረጃ የሚይዙት 19 ሚሊዮን ዶላር፣ ከ9ኛ እስከ 16ኛ ደረጃ ላይ የሚቀመጡት 15 ሚሊዮን ዶላር፣ ከ17ኛ እስከ 32ኛ ደረጃ ያላቸው ቡድኖች 11 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ከ33ኛ እስከ 48ኛ ደረጃ ይዘው የሚያጠናቅቁት አገራት እያንዳንዳቸው 9 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት ገንዘብ ያገኛሉ። በተጨማሪም በእያንዳንዱ ደረጃ ላይ ለሚገኙት ቡድኖች ከሚሰጠው የሽልማት ገንዘብ ውጪ፣ ለእያንዳንዱ ተሳታፊ አገር ለዝግጅት ወጪ (Preparation costs) 1.5 ሚሊዮን ዶላር ተመድቦ የነበረ ሲሆን፤ በዚህም ማንኛውም ተሳታፊ አገር ቢያንስ 10.5 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቱ ተረጋግጦ ነበር። ነገር ግን ምክር ቤቱ ውድድሩ ከመጀመሩ 44 ቀናት በፊት፣ እ.አ.አ ኤፕሪልክ 2026 በቫንኩቨር ካናዳ ባደረገው ሌላኛው ስብሰባው ተጨማሪ ማሻሻያ አድርጓል። ውድድሩ ባስመዘገበው ከፍተኛ የንግድ ገቢ ምክንያት፣ ምክር ቤቱ ቀደም ሲል አጽድቆት በነበረው በጀት ላይ ተጨማሪ የ15 በመቶ ጭማሪ በማድረግ አጠቃላይ ድምሩን ወደ 871 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ አድርጎታል። በዚህ የቫንኩቨር ስብሰባ በተወሰነው አዲስ ማሻሻያ መሠረት፦ ለእያንዳንዱ አገር የሚሰጠው የዝግጅት ወጪ (Preparation money) ከ1.5 ሚሊዮን ዶላር ወደ 2.5 ሚሊዮን ዶላር እንዲያድግ ተደርጓል። ለውድድር ተሳትፎ (Qualification money) ከ9 ሚሊዮን ዶላር ወደ 10 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ብሏል። ይህም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ 48 አገራት በሚሳተፉበት በዚህ የዓለም ዋንጫ ላይ የሚሳተፍ ማንኛውም አገር፣ ከምድብ ማጣሪያው ባያልፍ እንኳ በትንሹ 12.5 ሚሊዮን ዶላር (የ2.5 ሚሊዮን ዝግጅት እና የ10 ሚሊዮን የተሳትፎ ክፍያ) ያገኛል። በተጨማሪም ለቡድኖች ልዑካን ቡድን ወጪ መሸፈኛ እና ለትኬት ድልድል ከ16 ሚሊዮን ዶላር በላይ ተጨማሪ ድጎማ መመደቡ ተገልጿል። የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በጉዳዩ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ ፊፋ በአሁኑ ወቅት በታሪኩ እጅግ ጠንካራ በሆነ የፋይናንስ አቋም ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ ይህም ሁሉንም አባል ማኅበራት ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ለመደገፍ እንዳስቻለ ገልጸዋል። ይህ ውሳኔም የፊፋ ሀብት እንዴት በቀጥታ ወደ እግር ኳሱና ለዘርፉ ዕድገት መልሶ ጥቅም ላይ እንደሚውል የሚያሳይ ትልቅ ማረጋገጫ ነው ብለዋል። ከተሳታፊ ቡድኖች ክፍያ የተረፈው አጠቃላይ ገቢ፣ በ211 የፊፋ አባል ማኅበራት አማካኝነት ለዓለም እግር ኳስ ዕድገት ማስፈጸሚያ በድጋሚ ጥቅም ላይ እንደሚውል ፊፋ አስታውቋል።
ኮትዲቯር ወደ ጥሎ ማለፍ ለመግባት ከኩራሳኦ ጋር ትጫወታለች
Jun 25, 2026 187
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ አምስት መርሐ ግብር ኮትዲቯር ከኩራሳኦ ጋር ጨዋታዋን ታከናውናለች። ጨዋታው ምሽት አምስት ሰዓት ላይ በፊላደልፊያ ስታዲየም ይካሄዳል። ከሁለት ጨዋታዎች ሶስት ነጥብ ያገኘችው ኮትዲቯር ማሸነፍ ቀጥታ ወደ ጥሎ ማለፍ ያስገባታል። አቻ መውጣት በምርጥ ሶስተኝነት ሊያሳልፋት ይችላል። በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን እያደረገች የምትገኘው ኩራሳኦ በአንድ ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ኩራሳኦ ወደ ጥሎ ማለፍ ለመግባት ያላት ብቸኛ እድል ማሸነፍ ብቻ ነው። በዚሁ ምድብ ኢኳዶር ከጀርመን በኒው ዮርክ ኒው ጀርሲ ስታዲየም ከምሽቱ አምስት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አኳዶር በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዛለች። የአራት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ጀርመን በስድስት ነጥብ ጥሎ ማለፍ መግባቷን አረጋግጣለች። የደቡብ አሜሪካዋ ኢኳዶር ወደ ጥሎ ማለፍ የመግባት ተስፋውን ለማለምለም ጨዋታውን ማሸነፍ ይጠበቅባታል። በተያያዘም በምድብ ስድስት የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ቱኒዚያ ከኔዘርላንድስ ከሌሊቱ ስምንት ላይ በካንሳስ ሲቲ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። በምድቡ ሁለት ጨዋታዎች የተሸነፈችው እና ከውድድሩ የተሰናበተችው ቱኒዚያ የመርሐ ግብር ማሟያ ጨዋታዋን ታደርጋለች። በአራት ነጥብ ምድቡን የምትመራው ኔዘርላንድስ ካሸነፈች ወይም አቻ ከወጣች ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቷን ታረጋግጣለች። በዚሁ ምድብ ጃፓን ከስዊድን ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ በዳላስ ስታዲየም ይጫወታሉ። ጃፓን በአራት ነጥብ ሁለተኛ፣ ስዊድን በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። ጃፓን ማሸነፍ ወይም አቻ መውጣት ወደ ቀጣዩ ዙር ያሳልፋታል። በአንጻሩ ስዊድን ካሸነፈች በቀጥታ ወደ ቀጣዩ ዙር ታልፋለች። አቻ መውጣትም በምርጥ ሶስተኝነት ሊያሳልፋት ይችላል። በምድብ አራት በተመሳሳይ ሁለት ጨዋታዎች ከሌሊቱ 11 ሰዓት ላይ ይደረጋሉ። ቱርኪዬ ከአሜሪካ በሎስ አንጀለስ ስታዲየም ይጫወታሉ። በምድቡ በሁለት ጨዋታ የተሸነፈችው ቱርኪዬ ከውድደሩ መሰናበቷ ይታወቃል። በአንጻሩ ከአዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው አሜሪካ በስድስት ነጥብ ወደ ጥሎ ማለፉ ገብታለች። በሌላኛው የምድቡ መርሐ ግብር ፓራጓይ ከአውስትራሊያ በሳን ፍራንሲስኮ ቤይ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አውስትራሊያ እና ፓራጓይ በተመሳሳይ ሶስት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበላልጠው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። ማሸነፍ ሀገራቱን ወደ ጥሎ ማለፉ ያስገባቸዋል። አቻ መውጣት አውስትራሊያን በቀጥታ ወደ ቀጣዩ ዙር እንድታልፍ ያስችላታል። ፓራጓይ ከጨዋታው አንድ ነጥብ ካገኘች በምርጥ ሶስተኝነት የማለፍ እድል ይኖራታል።
ሞሮኮ እና ደቡብ አፍሪካ ወደ ጥሎ ማለፍ ተሸጋግረዋል
Jun 25, 2026 238
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የምድብ አንድ እና ሶስት የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዎች ከእኩለ ሌሊት በኋላ ተደርገዋል። በአትላንታ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ ሶስት ጨዋታ ሞሮኮ ሃይቲን ከመመራት ተነስታ 4 ለ 2 አሸንፋለች። አሽራፍ ሀኪሚ፣ እስማኤል ሳይባሪ፣ ሶፊያን ራህሚ እና ጌሲም ያሲን ግቦቹን አስቆጥረዋል። እስማኤል ሳይባሪ በውድድሩ ላይ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ሶስት አድርሷል። ዊልሰን ኢሲዶር እና የሞሮኮው ግብ ጠባቂ ያሲን ቦኖ በራሱ ላይ የሃይቲን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ሞሮኮ በሰባት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ጥሎ ማለፍ ገብታለች። ሞሮኮ በዓለም ዋንጫው ታሪክ ግማሽ ፍጻሜ የገባች የመጀመሪያ አፍሪካዊት ሀገር መሆኗ ይታወቃል። አስቀድማ ከውድድሩ የተሰናበተችው ሀይቲ ያለ ምንም ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። በሚያሚ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ ሶስት ሌላኛው መርሐ ግብር ብራዚል ስኮትላንድን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ሺኒሸስ ጁኒየር ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ማትያስ ኩንሃ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ቪኒሸስ ጁኒየር በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት አራት አድርሷል። በጉዳት ላይ የነበረው ኔይማር ተቀይሮ በመግባት የመጀመሪያ የዓለም ዋንጫ ጨዋታውን አድርጓል። ውጤቱን ተከትሎ ብራዚል በሰባት ነጥብ የምድቡ መሪ በመሆን ጥሎ ማለፍ ገብታለች። ስኮትላንድ በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን ምርጥ ሶስተኛ ሆና ለማለፍ የሌሎች ምድቦችን ውጤት ትጠብቃለች። በተያዘዘም በምድብ አንድ የምትገኘው ደቡብ አፍሪካ ኮሪያ ሪፐብሊክን 1 ለ 0 አሸንፋለች። በሞንቴሬይ ስታዲየም በተካሄደው ታፔሎ ማሴኮ በ63ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ድሉን ተከትሎ ደቡብ አፍሪካ በአራት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለጥሎ ማለፉ አልፋለች። ኮሪያ ሪፐብሊክ በሶስት ነጥብ ሶሶተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ ለማለፍ የሌሎቹን ምድቦች ውጤት ትጠብቃለች። በዚሁ ምድብ በሜክሲኮ ሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሜክሲኮ ቼክ ሪፐብሊክን 3 ለ 0 አሸንፋለች። ማቲዮ ቻቬዝ፣ ጁሊያን ኪኖኔስ እና አልቫሮ ፊዳልጎ ግቦቹን አስቆጥረዋል። አስቀድማ ወደ ጥሎ ማለፉ መግባቷን ያረጋገጠችው ሜክሲኮ በዘጠኝ ነጥብ የምድቡ መሪ ሆና አጠናቃለች። በዓለም ዋንጫው ሁሉንም የምድቧን ጨዋታ ያሸነፈች ብቸኛ ሀገር ሆናለች። ሜክሲኮ ከዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ ናት።
ስዊዘርላንድ፣ ካናዳ እና ቦሲኒያ ሄርዞጎቪና ጥሎ ማለፉን ተቀላቀሉ
Jun 25, 2026 186
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ ሁለት የመጨረሻ ጨዋታዎች ትናንት ማምሻውን ተደርገዋል። በቢሲ ፕሌስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ስዊዘርላንድ ካናዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ሩበን ቫራጋስ እና የካናዳው ጆሃን ማዛምቢ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ፕሮሚስ ዴቪድ የካናዳን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ ስዊዘርላንድ በሰባት ነጥብ የምድቡ መሪ በመሆን ወደ ጥሎ ማለፉ ገብታለች። ከአዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ካናዳ በአራት ነጥብ ተመሳሳይ ነጥብ ያላትን ቦሲኒያ ሄርዞጎቪናን በግብ ክፍያ በልጣ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥሎ ማለፉን መግባቷን አረጋግጣለች። በዚሁ ምድብ በሲያትል ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው ጨዋታ ቦሲኒያ ሄርዞጎቪና ኳታርን 3 ለ 1 አሸንፋለች። ከሪም አላጅቤጎቪች፣ ኤርሚን ማህሚች እና የኳታሩ ሱልጣን አል ብሬክ በራሱ ላይ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ሀሰን አል ሃይዶስ የኳታርን ብቸኛ ጎል አስቆጥሯል። ቦሲኒያ ሄርዞጎቪና በአራት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ በምርጥ ሶስተኛነት ወደ ጥሎ ማለፍ ገብታለች። ኳታር በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ በመያዝ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉትን ችግኞች የመንከባከብ ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል
Jun 25, 2026 82
ግምቢ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):-በምዕራብ ወለጋ ዞን በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉትን ችግኞች ለመንከባከብ ስራ ትኩረት መሰጠቱን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ። የምዕራብ ወለጋ ዞን አመራሮች እና የዞኑ ነዋሪዎች የተሳተፉበት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በመንዲ ከተማ ዛሬ ተጀምሯል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፈ እንዳሉት፤ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄን ስኬታማ ለማድረግ የተተከሉ ችግኞችን በአግባቡ መንከባከብ ከሁሉም ይጠበቃል። ለመርሃ ግብሩ ስኬታማነትም እንደ ዞን በቂ የችግኝ ዝግጅት፣ ተገቢው የቦታ መረጣ እና የችግኝ መትከያ ጉድጓድ መቆፈሩን ገልጸዋል። በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከተዘጋጁት 328 ሚሊዮን ችግኞች ውስጥ ለምግብነት እና ለገቢ ምንጭ የሚያገለግሉ የፍራፍሬ፣ የቡና እና የእንስሳት መኖ ችግኞች ከፍተኛ ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን አቶ ተሊላ አስገንዝበዋል። ባለፉት ዓመታት በመርሃ ግብሩ የተተከሉ ችግኞች አብዛኛዎቹ ጸድቀው ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ማስገኘታቸውንም ዋና አስተዳዳሪው አረጋግጠዋል። ከመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች መካከል አባገዳ አምቢሳ ሊካሳ በሰጡት አስተያየት፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን እንደ ሰው ልጅ ተንከባክቦ ማሳደግ የትውልዱ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል። በየዓመቱ አሻራቸውን በማኖራቸው ልዩ ደስታ እንደሚሰጣቸው ገልጸው፣ ችግኞችን ከመትከል ባሻገር የጽድቀት ሂደታቸውን በአግባቡ እንደሚከታተሉም ተናግረዋል። አቶ ኤሊያስ ቱቾ በበኩላቸው፤ ችግኝ መትከል በርካታ ጠቀሜታ እንዳለው በመገንዘብ በችግኝ ተከላው እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በየዓመቱ በችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የተናገረው ደግሞ ወጣት ኩርፈሳ ኦልጂራ ነው። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ከ200 በላይ የፍራፍሬ ችግኞችን በግሉ ለመትከል ማቀዱንም ጠቁሟል።
ችግኞችን አዘጋጅተን በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችን አድጓል-ወጣቶች
Jun 25, 2026 77
ሀዋሳ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ለአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና ለኮሪደር ልማት የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች አዘጋጅተው በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን በችግኝ ብዜት ሥራ የተሰማሩ ወጣቶች ተናገሩ። በክልሉ የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች አዘጋጅተው በማቅረብ ሥራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው ባለፈ የተራቆቱ መሬቶች እንዲያገግሙም በማድረግ በኩልም አስተዋጾ እያደረጉ ነው። በተለይ ለአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ስኬታማነት ወጣቶች በማህበር ተደራጅተው ችግኞችን እያቀረቡና የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እየሆኑም መጥተዋል። በማህበር ተደራጅተው የፍራፍሬ፣ የውበትና የጥላ ዛፍ ችግኞችን አዘጋጅተው በማቅረብ ተጠቃሚ ከሆኑ ወጣቶች መካከል የድሪመርስ ላንድ ስኬፒንግና ሲድሊንግ ማህበር አባላት ይገኙበታል። የማህበሩ ሥራ እስኪያጅ ኮከብ ቢያድግልኝ (ዶ/ር) አምስት ሆነው በ50 ሺህ ብር መነሻ ካፒታል የችግኝ ማፍላትና ማቅረብ ሥራቸውን ጀምረው በአሁኑ ወቅት ካፒታላቸውን 500 ሺህ ብር ማድረስ ችለዋል። በስራቸው የማህበሩ አባላት ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን የገለጸችው ኮከብ (ዶ/ር)፣ በአሁኑ ወቅትም ለሌሎች አምስት ሰዎች የሥራ ዕድል መፍጠር እንደቻሉም ተናግራለች። በማህበሩ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል ወጣት ባዩ በየነ እንዳለው፣ በማህበሩ በተፈጠረለት የሥራ ዕድል ገቢ እያገኘ ራሱን ማስተዳደር ችሏል። የሲዳማ ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አበባየሁ በየነ እንዳሉት፣ በክልሉ በየዓመቱ በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የተለያዩ ችግኞችን በመትከል የተራቆቱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙና የግብርና ምርታማነት እንዲጨምር ለማድረግ እየተሰራ ነው። በዘንድሮው የክረምት አረንጓዴ አሻራ መረሀ ግብር የፍራፍሬ፣ የቡና፣ የቀርከሃና ሌሎች አገር በቀል ዝርያ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጎ ወደተግባር መገባቱን ገልጸዋል። በክልሉ በክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎችን ለማሳተፍ መታቀዱን ጠቅሰዋል። ለተከላ ከተዘጋጁት ችግኞች ውስጥ አቮካዶ፣ አፕል፣ ማንጎ፣ ቡናና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች እንዲሁም ቀርከሀ፣ ቀረሮ፣ ዋንዛና መሰል ሀገር በቀል ችግኞች ይተከላሉ ብለዋል። ችግኞቹ በ316 የመንግስት፣ የማህበራትና አርሶ አደሮች የችግኝ ጣቢያዎች መዘጋጀታቸውን የተናገሩት አቶ አበባየሁ፣ ይህም አርሶ አደሩ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ ከማድረግ ባለፈ ለሥራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል። በአረንጓዴ አሻራ የሚተከሉት የፍራፍሬ ችግኞች በቀጣይ ለምርት ሲደርሱ ለኢንዱስትሪ ፓርክ ግብዓት እንዲሆኑ ታስቦ የተዘጋጁ መሆኑንም ገልጸዋል።
ርዕስ መስተዳድር አረጋ ከበደ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን በሰሜን ጎጃም ዞን በመገኘት አስጀመሩ
Jun 25, 2026 108
ባህርዳር፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አረጋ ከበደ የዘንድሮውን የክረምት አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን በሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ እንጉቲ ቀበሌ በመገኘት አስጀምረዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ባስጀመሩት የዘንድሮው ክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል መሐመድ ተሰማ ተገኝተዋል። በክልሉ በክረምቱ ወቅት ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተዘጋጅተዋል። በክልሉ ባለፉት ሰባት ዓመታት ህብረተሰቡን በማሳተፍ በተካሄደ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የደን ሃብት ሽፋኑን ከማሻሻል ባለፈ የአፈር መከላትን ማስቀረት እንዲሁም የተፈጥሮ ሚዛንን መከላከል መቻሉም ተመላክቷል። አርሶ አደሩም ተፋሰሶች በመልማታቸው በመስኖ፣ በእንስሳት ማድለብና ማርባት፣ በንብ ማነብ፣ በመኖ ልማትና በሌሎች የግብርና ዘርፎች ምርታማነቱን ለማሳደግ ችሏል። የተገኘውን ጥቅም አጠናክሮ ለማስቀጠልም በዘንድሮው ክረምት ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ የደን፣ የፍራፍሬና የውበት ችግኞችን በማዘጋጀት መርሃ ግብሩን አስጀምረዋል። የተዘጋጀውን ችግኝም ህብረተሰቡን በማሳተፍ በ261 ሺህ 460 ሄክታር መሬት ላይ በመትከል የመንከባከብ ስራ ይሰራልም ተብሏል። በችግን ተከላ ፕሮግራሙ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የመከላከያና ሌሎች የክልል አመራሮች ተሳትፈዋል።
የጅማ ከተማ ወጣቶች በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሥራ ዕድል አግኝተዋል
Jun 25, 2026 106
ጅማ፤ ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ እየተከናወነ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን የጅማ ከተማ ወጣቶች ገለጹ። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች ወጣት ሒካ መኮንን፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ሥራ በቤተሰቦቹ ላይ ጥገኛ እንደነበር ተናግሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሕይወቱ ትልቅ ተስፋ እንደሆነለት ይገልጻል። ወጣት ሒካና ጓደኞቹ በማኅበር ተደራጅተው ችግኝ በማፍላት ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማዘጋጀት በየዓመቱ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግሯል። በተለይም ከዚህ ቀደም ለከተማ ውበት ተብለው ከሌሎች አካባቢዎች ይመጡ የነበሩ ችግኞችን እያፈሉ በስፋት እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላው ወጣት አብዱልከሪም ያሲን በበኩሉ በችግኝ ማፍላት ሥራ በሚያገኘው ገቢ ራሱን እያስተዳደረበት መሆኑን ተናግሯል። በትጋት ሠርተን የተለያዩ የፍራፍሬና ለከተማ ውበት የሚሆኑ ችግኞችን ማዘጋጀታችን ተመራጭ እንድንሆን አድርጎናል፤ ወደፊትም ይህንን በማጠናከር ይበልጥ ተጠቃሚ ለመሆን እንሠራለን ብለዋል። ሌላኛው ወጣት እስማኤል ቦሪ ደግሞ በአረንጓዴ አሻራ በተፈጠረለት የሥራ ዕድል ከራሱ አልፎ ቤተሰቦቹን ማገዝ መቻሉን ገልጾ፤ አረንጓዴ አሻራ ንጹሕ አየር ከመስጠት ባለፈ፣ የሥራ ዕድልና የሀገርን ኢኮኖሚ የሚደግፍ ትልቅ አቅም ነው ብሏል። የጅማ ከተማ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቶፊቅ ጊዲ፣ ወጣቶች በአረንጓዴ አሻራ የሥራ ዕድል ከማግኘት ባለፈ፣ ለከተማዋ ውበትና ገጽታ ግንባታ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በ12 ማኅበራት የተደራጁ ወጣቶች የዚህ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው፣ ለሥራቸው የሚረዱ አስፈላጊ ድጋፎችን የማድረግ ሥራም እየተከናወነ እንደሚገኝ አክለዋል። በጅማ ከተማ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 3 ነጥብ 8 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱ ታውቋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 11981
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 8645
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 7464
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 7362
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የጤና ነገር
Jun 24, 2026 1225
በዮሐንስ ደርበው የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ከተከሰተ በኋላስ የሚድንበት ዕድል ይኖራል? · ኪንታሮት እንዴት ይከሰታል? አጠቃላይ የቀዶ ጥገና ሐኪም የሆኑት ዶክተር ቤተልሔም አበራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በፊንጢጣ ውስጥ የሚገኙ በጤናማ መንገድ ፊንጢጣ እንዲዘጋ (‘ኩሽን’ እንዲሆን) የሚያደርጉ ደም ሥሮች በተለያየ ምክንያት ሲያብጡ ኪንታሮት (ሄሞሮይድ) ተከሰተ እንደሚባል አስረድተዋል። · የኪንታሮት በሽታ መንስዔ ይታወቃል? እንደ ሕክምና ባለሙያዋ ገለጻ ለኪንታሮት በሽታ መንስዔ ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል፤ የሰገራ ድርቀት በዋናነት ይነሳል። በተጨማሪም ይላሉ፤ በተለይም ሴቶች ላይ በእርግዝና ወቅት የጽንሱ መጠን (ክብደት) እየጨመረ በሚሄድበት ጊዜ ወደ መቀመጫ በሚያደርገው ጫና ምክንያት በፊንጢጣ ውስጥ የሚገኙ የደም ሥሮች እንዲያብጡ በማድረግ ለኪንታሮት መከሰት መንስዔ ይሆናል። በአሁኑ ጊዜ በስፋት ለሚከሰት የኪንታሮት በሽታ በመንስዔነት የሚነሳው ከመጠን ያለፈ ውፍረት መጨመር መሆኑንም ጠቁመዋል። ይህም ውፍረት ወደ መቀመጫ ጫና በማሳደር በፊንጢጣ ውስጥ ያሉ የደም ሥሮች እንዲያብጡ በማድረግ ኪንታሮት እንዲከሰት ያደርጋል ነው ያሉት። በሌላ በኩል እንደ ሥራ ባሕርያቸው ለረጂም ሠዓታት የሚቀመጡ ሰዎች ስለማይንቀሳቀሱና ይህን ተከትሎም ለድርቀት ስለሚጋለጡ ለኪንታሮት በሽታ ይዳረጋሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። ከአመጋገብ ዘይቤ ጋር በተያያዘም፤ በቂ ውኃ አለመጠጣት እና በፋይበር የበለጸጉ ምግቦችን አለማዘውተር ለድርቀት ስለሚዳርግ የኪንታሮት በሽታ እንዲከሰት ያደርጋል ብለዋል። ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) የጡት ካንሰርን መከላከል ይቻላል? · የኪንታሮት በሽታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ ያለው ለምንድን ነው? ኪንታሮት የተለመዱ (‘ኮመን’) ከሚባሉ የቀዶ ሕክምና በሽታዎች መካከል አንዱ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ቤተልሔም፤ በትክክል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን መረጃ ለጊዜው መግለጽ ባይቻልም በዓለም አቀፍ ደረጃ እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ የኪንታሮት ተጠቂ እንደሆነ ጠቁመዋል። እዚህ ላይ ልብ መባል ያለበት ጉዳይ የኪንታሮት በሽታ ከቦታ ቦታ ከሀገር ሀገር እንደሚለያይ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለዚህም ምክንያቱ ከውፍረት እና ለድርቀት ከሚያጋልጡ አመጋገቦች መዘውተር ጋር የተያያዘ በመሆኑ ነው ይላሉ። ለምሳሌ፡- በጣም ወፍራም ሰዎች በሚበዙባቸው እና ለድርቀት አጋላጭ ምግቦች በሚዘወተሩባቸው አካባቢዎች የኪንታሮት ተጋላጭነት ከፍተኛ ነው ይላሉ። የኪንታሮት በሽታ እየጨመረ (እየተስፋፋ) የሚሄድበት ምክንያትም ከአኗኗር ዘይቤ ጋር እንደሚያያዝ ገልጸው፤ ለምሳሌ አብዛኛውን ጊዜ ቁጭ ብሎ (ተቀምጦ) ማሳለፍ ለኪንታሮት አጋላጭ መንስዔ ነው ብለዋል። በተለይም ቢሮ አካባቢ የሚሠሩ ሰዎች ለበርካታ ሠዓታት ስለሚቀመጡ፣ ሥራ ሲበዛባቸውም ወደ መጸዳጃ ቤት መሄድ ባለባቸው ሠዓት ባለመሄድ (የሚሄዱበትን ጊዜ ስለሚያራዝሙ፣ ቆይ ይችን ልጨርስ…ትንሽ…የተወሰነ ደቂቃ እያሉ ማራዘም) ሰገራን ለድርቀት ያጋልጣል፤ ይህም የደም ሥሮች እንዲያብጡና ከፊንጢጣ ውጭ እንዲወጡ በማድረግ ለኪንታሮት መከሰት ያጋልጣል ብለዋል። · የኪንታሮት በሽታ ምልክቶች በፊንጢጣ ላይ ዕብጠት መኖር፣ መድማት፣ ማሳከክ እና የህመም ስሜት መኖር ከምልክቶቹ መካከል መሆናቸውን ዶክተር ቤተልሔም ያብራራሉ። የኪንታሮት በሽታ የውስጠኛው እና የውጨኛው ተብሎ እንደሚከፈል በመግለጽ፤ የበሽታው ደረጃም ከአንድ እስከ አራተኛ እንደሚመደብ ያስረዳሉ። ይህን ሲያብራሩም፤ በውስጠኛው የኪንታሮት በሽታ ባብዛኛው ህመም አይኖርም፣ የፊንጢጣ ደም ሥሮች ዕብጠትና መድማት ይኖራል፤ በውጨኛው የኪንታሮት በሽታ ግን የህመም ስሜት ይኖራል ይላሉ። · የኪንታሮት በሽታ ደረጃዎች ደረጃዎቹን በተመለከተ ሲያስረዱ፤ ምልክቶቹን እንዳስተዋሉ ቶሎ ወደ ሕክምና ባለመሄድ ከአንደኛ ወደ ሁለተኛ ከዚያም ወደ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ እየተባባሰ እንደሚሸጋገር ገልጸዋል። ስለዚህ ሰዎች ምልክቶቹን እንዳዩ ቢታከሙ ደረጃው ከፍ ሳይል በሽታውን የመግታት ዕድል ይኖራቸዋል ነው የሚሉት። የመጀመሪያ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ በዚህ ወቅት የኪንታሮት ህሙማን እንኳን የዕብጠቱን መኖር ባብዛኛው በእጃቸውም ነክተው እንደማያውቁት እና የመድማት ምልክት ሊኖር እንደሚችል ተናግረዋል። ሁለተኛ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ በዚህኛው ደረጃ ደግሞ ህሙማኑ በሚጸዳዱበት ወቅት ዕባጩ ወደ ውጭ እንደሚወጣ እና ሲጨርሱ በራሱ ጊዜ ዕባጩ ወደ ቦታው እንደሚመለስ አስገንዝበዋል። ሦስተኛ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ በሽታው ያለባቸው ሰዎች በሚጸዳዱበት ወቅት ወደ ውጭ የሚወጣውን ዕባጭ በእጃቸው ወደ ውስጥ ካላስገቡት በራሱ ጊዜ የማይመለስበት ደረጃ መሆኑን ይገልጻሉ። አራተኛ ደረጃ የኪንታሮት በሽታ፤ ይህ ደረጃ ዕባጩ ከፊንጢጣ ውጭ ይወጣና ተገፍቶም ወደ ውስጥ መግባት የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለ የኪንታሮት በሽታ፤ ያለ ቀዶ ሕክምና ሰዎች እቤታቸው እንዲያደርጉ የሚመከሩትን ሁኔታዎች በአግባቡ ካደረጉ ወደ ቀጣዩ ደረጃ እንዳይሸጋገር ማድረግ ይቻላል ይላሉ። · በወቅቱ ካልታከመ በአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ኪንታሮትን ከላይ በተገለጹ የኑሮ እና አመጋገብ ዘይቤዎች ማስተካከል እንደሚቻል (ወደ ቀጣዮቹ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ሳይሸጋገር ባለበት እንዲቆይ) ማድረግ እንደሚቻል ያስረዳሉ። ወደ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ከደረሰ ግን የቀዶ ሕክምና እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ ይህ ደግሞ ጥቅምም የጎንዮሽ ጉዳትም እንዳለው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም በመጀመሪያዎቹ ደረጃዎች ካልታከመ እና ወደ መጨረሻዎቹ ደረጃዎች ከደረሰ ከፍተኛ የደም መፍሰስ እንደሚኖረውና ይህም ከሰው ደም እስከመለገስ ሊያደርስ እንደሚችል ይገልጻሉ። ወደ ውጭ ወጥተው በሚቀሩ የፊንጢጣ ደም ሥሮች ውስጥ የደም መርጋት ሊያጋጥም እንደሚችልና ይህም ከፍተኛ ህመም እንደሚያመጣ ተናግረዋል። በዚህም ድንገተኛ ሕክምና የመፈለግ ደረጃ ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ነው ያመላከቱት። · የኪንታሮት በሽታ ሙሉ በሙሉ ይድናል ወይስ አይድንም? በየትኛውም ደረጃ ላይ ያለ የኪንታሮት በሽታ በጊዜውና በአግባቡ ከታከመ ሙሉ በሙሉ እንደሚድን ዶክተር ቤተልሔም አረጋግጠዋል። በተለይም አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለ የኪንታሮት በሽታን ሰዎች እቤታቸው በሚያደርጉት ትሪትመንት (የአኗኗርና አመጋገብ ዘይቤያቸውን በማስተካከል) ሊያድኑት እንደሚችሉም አመላክተዋል። በተጨማሪም ወደ ሕክምና ተቋም ቢሄዱ፤ የሰገራ ማለስለሻ፣ ፊንጢጣ ላይ የሚቀባ የህመምና ዕብጠት መቀነሻ መድኃኒት እንደሚሰጥ በመግለጽ ይህ ከተስተካከለ የአኗኗር ዘይቤያቸው ብሎም በብዛት ውኃ ከመጠጣት ጋር ሲሠናሰል በመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ኪንታሮት የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑን አስገንዝበዋል። ይህንን አልፎ ወደ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ላይ ቢደርስ እንኳን የተለያዩ የቀዶ ሕክምና አማራጮች እንዳሉ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት እንደ ኪንታሮቱ መጠን ‘ረበርባንድ’ (ዕባጩን ዙሪያውን በመቋጠር በጊዜ ሂደት ደርቆ እንዲረግፍ የማድረግ ሕክምና) እና ኪንታሮቱን (የደም ሥሮቹን ዕባጭ) በቀጥታ በቀዶ ሕክምና በማውጣት ማከም ይቻላል፤ መዳንም ይቻላል ብለዋል። · ኪንታሮት እና ባሕላዊ ሕክምና ከላይ እንደገለጽነው (የኑሮ ዘይቤን ማስተካከል፣ ውኃ በብዛት መጠጣት፣ በፋይበር የበለጸጉ ምግቦችን ማዘውተር፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ) ከዚያም ዘመናዊ ሕክምና መከታተል ተገቢ መሆኑን የሕክምና ባለሙያዋ መክረዋል። በአንጻሩ በባሕል (በልማድ) ፊንጢጣ ውስጥ የሆነ ነገር መቅበር፣ ኪንታሮትን በግለት መተኮስ ለካፋ ችግር ሊያጋልጥ ስለሚችል ይህን ከማድረግ መቆጠብ ይመከራል ብለዋል። ምክንያቱም ለፊንጢጣ መጥበብ (በሚጸዳዱበት ጊዜ ለመሰንጠቅና መድማት) ብሎም ለመሰል የጎንዮሽ ጉዳቶች ሊዳርግ እንደሚችል አስረድተዋል። ኪንታሮት በአግባቡ በቀዶ ሕክምና ካልወጣ በባሕል (ልማድ) መነካካቱ ለባክቴሪያ እንደሚያጋልጥ፤ ባክቴሪያው ደግሞ ከፊንጢጣ አልፎ ወደ ሌሎች የሰውነት ክፍሎች (ለምሳሌ ወደ ታፋና አካባቢው) የሚዛመት መግል የያዘ ከፍተኛ ኢንፌክሽን ያጋልጣል ብለዋል። በዚህ ጊዜ ወደ ሕክምና ሲመጡ ሕክምናውን በጣም ከባድ (ውስብስብና አስቸጋሪ) ያደርገዋል ነው ያሉት። · የፊንጢጣ ካንሰርና የኪንታሮት በሽታ ቀደም ብለን እንዳነሳነው የኪንታሮት በሽታ ምልክቶች፤ ማሳከክ፣ ዕባጭ፣ መድማት እና ህመም ናቸው ያሉት ዶክተር ቤተልሔም፤ የፊንጢጣ ካንሰርም ተመሳሳይ ምልክቶች ይኖሩታል ይላሉ። ስለዚህ ማንኛውም ሰው በፊንጢጣ በኩል ደም ሲመለከት ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም እንዲሄድ መክረዋል። ምክንያቱም ይላሉ፤ በፊንጢጣ በኩል ደም የሚታየው አንድም በኪንታሮት በሽታ እንዲሁም በአንጀት ቁስለት፣ በፊንጢጣ ካንሰር፣ በጨጓራ ቁስለት እና በትልቁ አንጀት ካንሰር ምክንያት ሊሆን ስለሚችል ነው። ከመድማት በተጨማሪ የፊንጢጣ ቁስለት በስፋት ከታየ ካንሰር ሊሆን እንደሚችልም አመላክተዋል። ቁስለቱ ፊንጢጣ ውስጥ ስለሚሆን በእጅ መንካትና ማወቅ የማይቻልበት ሁኔታ እንደሚኖርም ጠቁመዋል። · ምክረ ሐሳብ ለኪንታሮት በሽታ ላለመጋለጥ ወይም ከመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ወደ ቀጣዮቹ ደረጃዎች እንዳይሸጋገር መንስዔዎቹን መቀልበስ ተገቢ መሆኑን በአጽንዖት አንስተዋል። በዚህም መሠረት ድርቀት እንዳይኖር ማድረግ ቀዳሚው መፍትሔ መሆኑን አስገንዝበዋል። ለዚህም በቂ ውኃ መጠጣት፣ ከ25 እስከ 30 ግራም ፋይበር በየቀኑ መውሰድ (በደንብ ፋይበር ያላቸው ምግቦችን መመገብ ለምሳሌ፡- ጎመን፣ ቆስጣ፣ ብርቱካን፣ ሙዝ፣ አፕል፣ ባቄላ፣ ገብስ፣ አጃ፣ ስንዴ) ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም ድርቀትን ለመከላከል ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባ በመግለጽ፤ በሥራ ባሕርያቸው ቢሮ ውስጥም ሆነ ሌላ ቦታ መቀመጥ የሚያበዙ ሰዎች በመሐል በመነሳት መንቀሳቀስ እንዲሁም ከሥራ ሲወጡ በእግር መሄድ (ዎክ ማድረግ) እና ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ማድረግ ለአንጀት እንቅስቃሴ ዕገዛ በማድረግ ድርቀት እንዳይኖር ይጠቅማቸዋል ብለዋል። ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያለባቸው ሰዎችም ክብደታቸውን እንዲቀንሱ መክረው፤ ይህ ሲሆን ከፊንጢጣ ውጭ የነበረው የደም ሥር ዕብጠት (የኪንታሮት በሽታ) ወደ ነባር ቦታው እንዲመለስ ወይም ባለበት እንዲቆይ (በይበልጥ ተገፍቶ እንዳይወጣ) ይረዳል ይላሉ። ከልማዳዊ ሕክምና በመራቅ ዘመናዊ ሕክምናን ቀዳሚ ምርጫ ለማድረግ በተለይም ቀድሞ መከላከል የሚቻልበትን ብልኀት ለማዳበር ስለ ኪንታሮት በሽታ በስፋት ግንዛቤ መፍጠር ተገቢ ነው ይላሉ። በፊንጢጣ በኩል ደም ሲታይ ሁሌም ኪንታሮት ላይሆን እንደሚችልና ካንሰር ሊሆን እንደሚችልም በመገንዘብ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ ወደ ሌሎች ደረጃዎች ሳይሸጋገር በማከም እንዲድን ማድረግ ተገቢ መሆኑን መክረዋል።
ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል
Jun 23, 2026 1653
በኢዜአ ዐይን…! በዮሐንስ ደርበው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ጥቅም ንጥልም ቀላልም አይደለም፤ በተለያዩ ዐውዶች ገዝፎ ይገለጣል እንጅ። ለአብነትም፤ የደን ሽፋንን በማሳደግ የዓየር ንብረት ተጽዕኖን በመቀነስ ብሎም በመከላከል፣ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ እንዲሁም በመከላከል ምርታማነትን በመጨመር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የከተማ ውበት መጠበቅን ጨምሮ የተለያዩ ጥቅሞችን በቀጥታ ለሰው ልጆች ይቸራል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ አረንጓዴ ዐሻራ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልጽግና አሠናሥሎ የሚያረጋግጥ ብሔራዊ ኢኒሼቲቭ ነው። የደን፣ የሰብልና ሁለንተናዊ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ወሳኝ የልማት አቅጣጫም ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት ጽንሰ ሐሳቡ ከችግኝ ተከላ የተሻገረው አረጓዴ ዐሻራ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ መነሻ፤ የተራቆተ አካባቢን ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ከማድረግ የላቀ ድርብርብ ግብ ያለው ሰፊ መርሐ-ግብር ነው። በዚህም መሠረት፤ እንደየ ሥነ-ምኅዳሩ የሚላመዱ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ላላቸው ችግኞች፣ ለደን ሽፋን ማደግ የጎላ ሚና ለሚኖራቸው ችግኞች፣ ለከተማ ውበትና ለማረፊያ ጥላ ለሚሆኑ ዛፎች፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የሚችሉ ዛፎች የሚተከሉበት ነው። ይህም አንድን አካባቢ አረንጓዴ ከማድረግ ልቆ በረሃማነትንና የዓየር ንብረት ተጽዕኖን በመቀነስ፣ ምርታማነትን በመጨመር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን በማሳደግ በቀጥታ ሕብረተሰቡን የሚጠቅም ትልቅ ኢኒሼቲቭ መሆኑን ያስረዳል። የተለያዩ ክፍላተ-ዓለማት አንድም በካፋ ቅዝቃዜ እንዲሁም መደበኛ የኑሮ ሁኔታን በሚያናጋ አደገኛ ሙቀት ብሎም በድንገተኛ ጎርፍ እና ሰደድ እሳት በሚታመሱበት ጊዜ፤ እነዚህንና መሰል ችግሮችን ቀድሞ ለማረቅ አንዱ መፍትሔ አረንጓዴ ዐሻራን በስፋት ማከናወን መሆኑ ይታመናል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነትና ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባለፉት ዓመታት በብርቱዎቹ ኢትዮጵያውያን ርብርብ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል፤ ውጤቱንም ሕዝቡ ዐይቷል። ከውጤቶቹ መከካልም ለአብነት፤ ከሀገራዊ ለውጡ በፊት 17 ነጥብ 2 በመቶ የነበረው የደን ሽፋን አሁን ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማደጉ፣ የምርታማነትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት መጨመር ብሎም ውብና አረንጓዴ ከተሞች መስፋፋት የሚሉት ይነሳሉ። በሕዝቡ ዘንድ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ተፈጥሮን የመንከባከብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የሀገርን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጉዳይ ጭምር ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል። የአረንጓዴ ዐሻራን ውጤት ላጣጣመ ሥራውን በንቃት እንዲከውን መካሪ ባያሻም፤ ካለፈው የበለጠ ውጤት እንዲገኝ ዛሬ ላይ ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚነታቸውን በሚያረጋግጠው የአረንጓዴ ዐሻራ በነቂስ መሳተፍ እና ባሕላቸው ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ከአረንጓዴ ዐሻራ ትሩፋቶች መካከል • በሰብል፣ ፍራፍሬ፣ ቡና ምርታማነት እና በሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን ያደረገው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ አሁን ዘርፈ-ብዙ ጥቅሙ በተጨባጭ እየተገለጠ ነው። ከበርካታ ትሩፋቶቹ መካከልም የምርታማነት ማደግ ተጠቃሽ ነው። ይህን ተከትሎም የሕብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አድጓል። ይህን ሐሳብ በአኃዝ አስደግፎ ብናየው፤ ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፊት (በ2010 ዓ.ም) በሔክታር የሚመረተው ስንዴ 22 ኩንታል፣ በቆሎ 30 ኩንታል፣ ጤፍ 17 ኩንታል እንዲሁም ገብስ 23 ኩንታል ነበር። ከኢንሼቲቩ ትግበራ በኋላ ደግሞ (በ2017 ዓ.ም) ስንዴ በሔክታር 36 ኩንታል፣ በቆሎ 46 ኩንታል፣ ጤፍ 20 ኩንታል፣ ገብስ 30 ኩንታል ማምረት ተችሏል። በዚህም መሠረት በ2017 ዓ.ም 7 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር መሬት በስንዴ ሰብል በመሸፈን 280 ሚሊየን ኩንታል ማምረት ተችሏል። ስንዴን በትጋት በማምረትም ከውጭ ለማስገባት ይወጣ የነበረን 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል። በሌላ በኩል ደግሞ፤ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፍራፍሬው ዘርፍ ዕድገትም ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል። በዚህም ገበያውን ከማረጋጋት ባለፈ ሕብረተሰቡ (አምራቹ) ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ በዚያው ልክ እንዲያድግ አስችሏል። ኢትዮጵያም በአፍሪካ አቮካዶን በቀዳሚነት ወደ ውጭ የምትልክ ሁለተኛዋ ሀገር እንድትሆን አስችሏታል። ሌላኛው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ትሩፋት የቡና ልማት መስፋፋትና የውጭ ምንዛሬ ማደግ ነው። ይህን በአሥረጂ አስደግፈን ብንመለከት፤ በ2011 ዓ.ም በ600 ሺህ ሔክታር ላይ ቡና ተተክሏል። 500 ሺህ ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል። 738 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኝቷል። እንዲሁም በ2017 ዓ.ም 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ቡና ተተክሏል። 1 ነጥብ 58 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል። 2 ነጥብ 65 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢም ማግኘት ተችሏል። እንዲሁም ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ጋር በተያያዘ ለ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል። ከላይ የተጠቀሱ ማሳያዎችን (ናሙናዎችን) ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በቀጥታ ለሕዝቡ ጥቅም የቆመ መርሐ-ግብር መሆኑን መገንዘብ አያዳግትም። ስለዚህ በቀጣይ ሕብረተሰቡ በዚህ ኢኒሼቲቭ ላይ ያለጠባቂነት በንቃት በመሳተፍ እና ባሕሉ በማድረግ ተጠቃሚነቱንም በዚያው ልክ ለማሳደግ መትጋት ይጠበቅበታል። እስከ ዓለም ከፍታ ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር የሚዳርገው ህመም ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ አበርክቶዎች መካከል • በመሬት መራቆት መቀነስ፣ በደን ሽፋን ማደግ፣ በውኃማ አካላት መስፋፋት ረገድ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ፤ የአካባቢ መራቆትን በመቀነስና በመቅረፍ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል፣ በደን መጨፍጨፍ ምክንያት ይከሰት የነበረን የበረሃማነት መስፋፋት ቀንሷል፣ የደን ሽፋንን ጨምሯል፣ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ መሬት እንዲያገግም በማድረግ ምርታማነትን ጨምሯል። በተጨማሪም የውኃማ አካላትን መመናመን ቀንሷል (ደርቀው የነበሩ ስፍራዎች ወደ ቀድሞ ውኃማ ይዘታቸው እንዲመለሱ አስችሏል)፣ የአካባቢ መራቆትና የዓየር ንብረት ፈተናዎችን በመቀነስ ረገድም የራሱን ከፍተኛ ሚና አበርክቷል። ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ትግበራዋ ስኬታማነት ዓለም ዕውቅና ችሯታል በሀገር አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማትና መሪዎች ዘንድ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ትግበራ ተወድሷል። ከእነዚህ ዕውቅናዎች መካከል፤ የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአግሪኮል ሽልማት መስጠቱ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) Outstanding African Leadership Award ማግኘታቸው የሚሉት ይጠቀሳሉ። እንዲሁም፤ ኢትዮጵያ 2ኛውን የአፍሪካ የዓየር ንብረት ጉባዔ ተመርጣ ማስተናገዷ፣ ኢትዮጵያ 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት የሥርዓተ-ምግብ ጉባዔ ማስተናገዷ፣ በ80ኛው የዓለም ምግብና እርሻ ድርጅት ጉባዔ ለዘላቂ ደን ልማት የተሰጣት ዕውቅና እንዲሁም ኢትዮጵያ ኮፕ-32 (COP- 32) ለማስተናገድ መመረጧ በዘርፉ ላከናወነችው አርዓያነት ያለው ተግባር የተሰጡ ዕውቅናዎች ናቸው። ኢትዮጵያ ስኬታማውን የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ትልሟን ለሀገራት ማጋራቷ ኢትዮጵያ በራሷ ሐሳብ አመንጭነት ሕዝቧን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እየተሰጠ ባለ ያልተቆራረጠ ጠንካራ አመራር በአረንጓዴ ዐሻራ ዘርፍ ያስመዘገበችውን ስኬት፣ አሠራር (ልምድ) እና ችግኝ ለተለያዩ ሀገራት አጋርታለች። ይህም እየሄድችበት ያለው መንገድ ሁሉ ተባብሮ ማደግን ያነገበ ለመሆኑ አሥረጂ ነው። በዚህም መሠረት፤ በ2012 ዓ.ም ለፑንትላንድ፣ በ2012 ዓ.ም ለፓኪስታን፣ በ2012 ዓ.ም ለጂቡቲ፣ በ2013 ዓ.ም ለደቡብ ሱዳን፣ በ2013 ዓ.ም ለሩዋንዳ እና ለሌሎችም በዘርፉ ያላትን የተመሠገነ ልምድ አጋርታለች። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ የተመራበት ሂደት የኢኒሼቲቩ ሐሳብ አመንጭ እና አመራር ሰጭ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ናቸው። ወደ ክልል፣ ዞን ወረዳ እና ቀበሌ በማውረድም በተቀናጀ ትጋት በመመራቱም ስኬታማ መሆን ችሏል። በዚህም መሠረት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነትና አመራር ሰጭነት፣ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች እና ባለድርሻ አካላት ቅንጅት፣ በክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮችና ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ቅንጅት፣ በየደረጃው በተዋቀረ የቴክኒክ ኮሚቴ አማካኝነት፣ በተደራጀ የሕዝብ ተሳትፎ አማካኝነት የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በስኬት እየተተገበረ ይገኛል። ከአረንጓዴ ዐሻራ ጋር በተያያዘዘ የቀጣይ አቅጣጫዎች የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ የለውጡ መንግሥት ከመጣ ወዲህ ላለፉት ዓመታት በተቀናጀ አግባብ ተመርቷል፤ አሁንም እየተተገበረ ነው። በቀጣይ ደግሞ ኢኒሼቲቩ እንዴት መከናወን እንዳለበት ግቦች ተቀምጠዋል። በዚህም መሠረት፤ የሕዝብ ባለቤትነትን አጠናክሮ ማስቀጠል (አረንጓዴ ባሕል መገንባት)፣ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎችን ማስፋትና በደን ላይ የሚደርሰውን ጫና መቀነስ፣ የሕግና የፖሊሲ ማሻሻያ የሚፈልጉ ጉዳዮችን ለይቶ በጥናት መመለስ የሚሉት የቀጣይ አቅጣጫዎች ናቸው። በተጨማሪም፤ ከአረንጓዴ ዐሻራ የሚገኘውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት አጠናክሮ ማስቀጠል፣ የባለድርሻ አካላት እና የተቋማት ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር፣ በክረምት ወራት የሚተከሉ ችግኞችን በበጋ ወራት በአግባቡ መንከባከብ ከቀጣይ አቅጣጫዎች መካከል ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በቢሾፍቱ ማስጀመራቸው ይታወቃል። በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክትም፤ ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞች ለተከላ ዝግጁ በሆኑበት በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ወቅት አረንጓዴ ለሆነች ነገ፣ ሁላችንም ተስፋን እንትከል ሲሉ ለሀገሬው ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ዘርፈ-ብዙ ጥቅሙ በተጨባጭ እየተገለጠ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2011 ዓ.ም መጀመሩም የሚታወስ ነው። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #ተስፋን_እንትከል
ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes)
Jun 23, 2026 936
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው · ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ሕጻናት ላይ የትኛው የስኳር ህመም ነው በስፋት እየተከሰተ ያለው? በሕጻናት ላይ የሚከሰቱ የተለያዩ የስኳር ህመም ዓይነቶች መኖራቸውን የሚገልጹት የሕጻናት የስኳር ህመም ስፔሻሊስት ዶክተር ሰውአገኝ የሺዋስ፤ እንደሀገራችን ግን በዋናነት የሚጠቀሰው ዓይነት አንድ የሚባለው የስኳር ህመም ነው ይላሉ። በአደጉ ሀገራት ላይ ዓይነት ሁለት የስኳር ህመምም በሕጻናት ላይ እንደሚከሰት ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም ባብዛኛው እንቅስቃሴ ካለማድረግ፣ ከኑሮ ዘይቤ እንዲሁም ከመጠን ባለፈ ውፍረትና ተያያዥ ጉዳዮች ምክንያት የሚከሰት መሆኑንም ያስረዳሉ። ይሁን እንጅ በእኛ ሀገር ደረጃ ይህ (ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም) በስፋት በሕጻናት ላይ እንደማይስተዋልና ብዙም አሳሳቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። በዋናነት በእኛ ሀገር ሕጻናት ላይ እየተከሰተ ያለው ዓይነት አንድ የስኳር ህመም መሆኑን ገልጸው፤ተገቢው ጥንቃቄ ባለመደረጉ ልጆች ለውስብስብ ችግር እየተዳረጉ ነው ብለዋል። እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የጡት ካንሰርን ለመከላከል ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? · ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም አጋላጭ ምክንያቱ ይታወቃል? እንደ ባለሙያው ገላጸ፤ ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም አጋላጭ መንስዔው አይታወቅም። ይህን ተከትሎም አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል ሕክምና የለም። እንደ አጋላጭ ከሚታሰቡት መከካል ግን፤ ልጆች በተፈጥሮ ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም የመጋለጥ ዕድላቸው ከፍተኛ መሆኑ እና ውጫው (አካባቢያዊ ሁኔታዎች) በምክንያትነት ይነሳሉ ብለዋል። በእነዚህ ምክንያቶች በእያንዳንዱ የሰውነት እንቅስቃሴ ውስጥ ስኳር እንዲዋሃድ የሚያደርገው ኢንሱሊን የተሰኘ ሆርሞን መመረቱ ይቆማል፤ የኢንሱሊን እጥረት ሲያጋጥም ደግሞ ስኳር ደም ላይ እየጨመረ ይሄዳል፤ ደም ከ180 በላይ ከፍ በጊዜም ኩላሊት ወደ ውጭ ያስወግደዋል፤ በዚሁ ወቅትም ጠቃሚ ንጥረ ቅመሞች ጭምር ከሰውነት ይወገዳሉ፤ የፈሳሽ እጥረትም ያጋጥማቸዋል፤ ከዚያም የልጆች የሰውነት ክብደት መቀነስና ቶሎ ቶሎ (ከመደበኛው የተለየ) የመሽናት ሁኔታ ይከሰታል ሲሉ አብራርተዋል። · ዓይነት አንድና ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም እንደ ዶክተር ሰዋገኝ ማብራሪያ፤ ዓይነት አንድ እና ዓይነት ሁለት የስኳር ህመሞች የተለያዩ ናቸው። ዓይነት አንድ የስኳር ህመም ማለት፤ ኢንሱሊን በሰውነት ውስጥ ሳይመነጭ ሲቀር የሚከሰት መሆኑን አስረድተዋል። ይህን ህመም ቀድሞ መከላከል አይቻልም፤ ሲከሰት ሕክምና ማግኘት እንጅ ይላሉ። ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም፤ ኢንሱሊን የማመንጨት ችግር ሳይሆን፤ ኢንሱሊኑ በሰውነት ውስጥ ሳይሠራ ሲቀር የሚከሰት ነው ይላሉ። ይህም ከሰውነት ክብደት መጨመር፣ አካላዊ እንቅስቃሴ ባለማድረግ ምክንያት የሚመጣ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲውም ብዙ ጊዜ በዐዋቂዎች ዘንድ በስፋት የሚስተዋል ህመም መሆኑንም አመላክተዋል። ይህን ህመም አመጋገብን በማስተካከል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ፣ የኑሮ ዘይቤን በማስተከከል ቀድሞ መከላከል እንደሚቻልም ነው ያስገነዘቡት። · የስኳር ህመም በየትኛው የዕድሜ ክልል ይከሰታል? ዓይነት አንድ የስኳር ህመም የ6 ወር ዕድሜ ካለው ሕጻን ጀምሮ እስከ በዐዋቂነት የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ዶክተር ሰውአገኝ ይናገራሉ። ይህን ሲያብራሩም በተለይም ከ30 ዓመት በታች ባሉት የዕድሜ ክልሎች (በተለይም ከ5 - 7 እንዲሁም ከ14 - 15 ዓመት) ባሉ ልጆች ላይ በስፋት ከሰታል ብለዋል። · ምልክቶቹ በውል ይታወቃሉ? በአብዛኛው ከተለመዱ ምልክቶች መካከል፤ ቶሎ ቶሎ ውኃ መጠጣት፣ የማይረካ የውኃ ጥማት መኖር፣ ከወትሮው የተለየ ሌሊትን ጨምሮ ሽንት የመሽናት፣ ክብደት መቀነስ የሚሉት እንደሚገኙበት ይገልጻሉ። እነዚህ ምልክቶች ሲታዩም ጊዜ ሳያባክኑ (ህመሙ ሥር ሳይሰድ) ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ ተገቢ መሆኑን መክረዋል። በዚህ ሂደት ልጆች ህመማቸውን ዐውቀውና ራሳቸውን ችለው ወደ ሕክምና ተቋም እንደማይሄዱ ስለሚታወቅ ወላጆች (አሳዲዎች) ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ሾተላይን ቀድሞ መከላከል ይቻላል? · ሕክምና እና ምክረ ሐሳብ ምንም እንኳ አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል የታወቀ ነገር ባይኖርም ዓይነት አንድ የስኳር ህመም፤ ቶሎ ከታወቀና ሕክምና ከተደረገለት ልጆች እንደማንኛውም ጤናማ ልጅ ዕድገታቸው ይቀጥላል፣ ትምህርታቸውን መማር፣ ኑሯቸውን መቀጠል ይችላሉ። ልጆች በጊዜው (ህመሙ እንደተከሰተ ወዲያውኑ) ካልታከሙ ሕይዎታቸውን እስከማጣት የሚደርስ ውስብስብ ችግር የሚፈጥር መሆኑን ገልጸው፤ ወላጆች (አሳዳጊዎች) የልጆቻቸውን ጤና በአግባቡ እንዲከታተሉ መክረዋል።የተለየ ምልክት ሲያስተውሉም ወደ ሕክምና መሄድን መክረዋል። ምንም እንኳን አመጋገብን ማስተካከል ለጤና እንደ ግብዓት ተጠቃሚ መሆኑ ቢታመንም፤ ዓይነት አንድ የስኳር ህመምን በአመጋገብ ብቻ እናስተካክላለን በሚል መዘናጋት ተገቢ እንዳልሆነ ሕብረተሰቡ ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል። በአመጋገብ ብቻ እናስተካክላለን ማለት ቶሎ እንዳይታከሙ ጊዜ በማባከን የልጆችን ጤና በይበልጥ ማወሳሰብ በመሆኑ፤ አዋጩ መፍትሔ በሕክምና ኢንሱሊን መስጠት እና በተጨማሪ አመጋገብን ከኢንሱሊኑ ጋር ማጣጣም መሆኑን አስገንዝበዋል። #የጤና_ነገር #ኢዜአ #ኢንሱሊን #የስኳር_ህመም #ሕጻናት
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Jun 21, 2026 1296
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 14/2018 (ኢዜአ) ፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? በሳምንቱ ቢሾፍቱ አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከባሕር ጠለል በላይ በ1 ሺህ 910 ሜትር ከፍታ ላይ በምትገኘው ቢሾፍቱ ግንባታው በመከናወን ላይ ይገኛል። የኤርፖርቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ግዙፍ የልማት ፕሮጀክት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የቢሾፍቱ ኢርፖርት ኢትዮጵያን ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ማዕከላት ተርታ ለማሰለፍ የሚያስችል ታሪካዊ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ሳምንት ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በስፍራው በመገኘት የግንባታውን ሂደት የተመለከቱ ሲሆን ግንባታውን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅም ሌሊትና ቀን በከፍተኛ ጥረት እየተገነባ ይገኛል ብለዋል። በእለቱም የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በቢሾፍቱ ያስጀመሩ ሲሆን ዘንድሮ የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞች የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጎሮ ወረዳ በመገኘት የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያስጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክትም ሀገራችንን በጋራ ማንሳት የምንችለው አንዳችን ለሌላችን እጃችንን ስንዘረጋ ብቻ ነው! ስለሆነም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በዚህ ሥራ እንዲሳተፍ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል። የሀገር መከታና የህዝብ አለኝታ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የህዝብ ወገንተኝነቱንና እና አለኝታነቱን በተግባር ማሳየቱን ቀጥሎበታል። ሰራዊቱ በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ ህዝባዊ ሰራዊት መሆኑን አሳይቷል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ተላላቅ መርሃ ግብሮች ባከበረበት ወቅት በሰሜን ጎንደር ዞን የ"ጭና ሰማዕታት መታሰቢያ ጤና ጣቢያ" ገንብቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ አስረክቧል። በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሰራዊቱ የጀግንነት ታሪክ እንደ ውቅያኖስ የማይነጥፍ ከመሆኑም በላይ፣ በጭና ግንባር የተቀዳጀው ድል የጠላትን ፖለቲካዊና ወታደራዊ አቅም ሙሉ በሙሉ የሰበረ የድል ማህተም ነው ብለዋል። ለልማት- የሃይል አማራጭን ማስፋት በኢትዮጵያ ከከተማ እስከ ገጠር የተሰናሰለ የሃይል ልማትን በማስፋት አማራጭ የሃይል አቅርቦት ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዚህ ሳምንትም በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ ከ312 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያስችል የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ለመገንባት መሰረተ ድንጋይ ተቀምጧል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሡልጣን ወሊ (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጥረት በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ለዘላቂ ልማትና ለዜጎች ተጠቃሚነት የሃይል አማራጭን የማስፋት ስራ ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አንስተዋል። በምርታማነት የምግብ ስርዓት ችግርን መፍታት በኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ችግርን ለመፍታት እስከ ታችኛው መንግስታዊ መዋቅር ድረስ የሚዘልቁ የተለያዩ ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በዚሁ መሰረትም በምግብ ስርዓት አለመስተካከል የሚከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገልጿል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት በክልሉ ስርዓት ምግብ ሽግግርና የቀዳማዊ ልጅነት ልማት ፍኖተ ካርታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄዷል። የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ችግር ፈች ምርምር ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በምርምር ሥራዎችና በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጸውም በዚህ ሳምንት ነው። በዩኒቨርሲቲው በምርምር ፕሮጀክቶች እና በማህበረሰብ አገልግሎቶች የተከናወኑ ተግባራትን ለመገምግምና ቅንጅታዊ ሥራን ለማጠናከር ያለመ መድረክም አካሄዶ ነበር። መድረኩ በተለይ ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶችን እውን ለማድረግና ዓለም አቀፍ ዕድሎችን አስፍቶ ለመጠቀም የተመራማሪዎችን አቅም ማሳደግ ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ ከ84 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ 54 የምርምር ሥራዎችን እንዲሁም 70 የማህበረሰብ አገልግሎቶችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። በቀብሪ በያህ ከተማ የወጣቶች የልማት ተጠቃሚነት በሶማሌ ክልል የልማትና የምርታማነት አጀንዳዎች በውጤታማነት ቀጥለዋል። የወጣችንና አጠቃላይ የክልሉን ህዝብ የልማት ፍላጎት መሰረት አድርገው እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው። በዚሁ መሰረት በክልሉ ፋፈን ዞን ቀብሪ በያህ ከተማ በማህበር ተደራጅተው ሥራ የፈጠሩ ወጣቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። አብዲከሪን መሀመድ እና ጓደኞቹ በማህበር ተደራጅተው በዶሮ እርባታ በመሰማራት በሌማት ትሩፋት የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል። ሥራውን ከጀመሩ ወዲህ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ ለሌሎች ወገኖችም ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙ ይናገራሉ። እንደ አጠቃላይ በሶማሌ ክልል ሰው ተኮር የልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ ቀጥለዋል። የበጀት ክለሳ በዚሁ ሳምንት የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የ2018 የበጀት ዓመት የ11 ወራት እቅድ አፈጻጸም መነሻ በማድረግ የቀረበለት የበጀት ክለሳ አፅድቋል። ካቢኔው በክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አማካኝነት የቀረበለትን ከ301 ሚሊየን 693 ሺህ 178 ብር የበጀት ክለሳ ነው ተወያይቶ ያፀደቀው። የበጀት ክለሳው በተለይም የፊስካልና ፋይናንሻል አፈፃፀማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ፕሮጀክቶችን በመለየት የላቀ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ላላቸውና የበጀት እጥረት ላጋጠማቸው ጉዳዮች የሚውል ነው ተብሏል። የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኢትዮጵያ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮቿን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት ልትሰጠው እየተጋች ነው። ለዚህ ዋና ማሳያው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ነው። ማዕከሉ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን የተገነባውን ኮንታ መሶብ የአንድ ማዕከል መርቀው በይፋ አገልግሎት አስጀምረዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል በተበታተነ ሁኔታ ይሰጡ የነበሩ የመንግሥትና የማኅበራዊ አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር በማሰባሰብ ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው። የኮንታ ማዕከልም ሕዝቡ ከቢሮ ወደ ቢሮ በመዘዋወር የሚያጠፋውን ጊዜ፣ ወጪና እንግልት በእጅጉ በመቀነስ ጥራት ያለው፣ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት እንዲያገኙ ያግዛቸዋል ተብሏል። የስደተኞች መጠጊያ- ኢትዮጵያ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞች መጠጊያ የሆነችው ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የስደተኞች ቀን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ተከብሯል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ክልሉ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞችን ከመቀበል ባለፈ ስደተኞችን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በክልሉ አራት መጠለያ ጣቢያዎች ላይ ከ112 ሺህ በላይ ስደተኞች እንደሚገኙ ገልፀው፥ ስደተኞች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ጠንካራ መስተጋብር በመፍጠር በአብሮነት እየኖሩ ነው ብለዋል። ስደተኞች የውሃ፣ የትምህርት የጤናና ሌሎች የመሠረተ ልማቶችን ከተቀባዩ ማህበረሰብ እኩል ተጠቃሚ መሆናቸው የኢትዮጵያን ስደተኞች አያያዝ የተሻለ ተሞክሮ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ጋምቤላ የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አባላት በመጪው የህዝብ ውክልና ስራ ስምሪት ወቅት የሚያከናውኗቸውን ተግባራት በተመለከተ የኦሬንቴሽን ፕሮግራም አካሂዷል። የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ጁል ናንጋል፣ የህዝብ ውክልና ተግባር የምክር ቤት አባላት ዋና ሃላፊነት መሆኑን ገልፀው፣ አባላቱ ወደ ህዝቡ በመቅረብ የህብረተሰቡን ፍላጎት፣ ችግርና አስተያየት በአግባቡ በማሰባሰብ ለመንግስት አካላት ማድረስ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። ምክትል አፈ ጉባኤው እንዳሉት፣ የህዝብ ውክልና ስራ በዜጎችና በምክር ቤቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እና የህዝብ ተሳትፎን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ያለው በመሆኑ አባላቱ በተሰጣቸው ኃላፊነት ትጋትና ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበዋል። ድሬደዋ ድሬደዋ የመስኖ ግንባታ። 'በቆላማ አከባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም' በሁላሁሉል ገጠር ቀበሌ ውስጥ የከርሰ ምድር ውሃን በመጠቀም የተሰሩ የንፁህ መጠጥ ውሃና የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች፥ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) በተገኙበት ተመርቋል። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) እና የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ ግድቡን በመረቁበት ወቅት ከምንም በላይ ለሰው ልጆች ህይወት እጅግ አስፈላጊ የሆነውና፥ የአስተዳደራችን የገጠር ነዋሪ ህብረተሰብ መሠረታዊ ፍላጎትና የረጅም ዘመናት ምኞት የነበረውን፥ የውሃ ጥያቄ በጋራ ርብርብ መመለስ መቻል የሚሰጠው ደስታ እጅግ ልዩ ነው ብለዋል ከንቲባው። የድሬዳዋን ማህበረሰብ የምግብ ሉኣላዊነት የማረጋገጥ፣ አርሶአደሩ ነዋሪ ከራሱ አልፎ ለገበያ በማቅረብ ኑሮውን እንዲያሻሽል እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የመስኖ ልማት ሥራዎችን እንዲያከናውን በማገዝ ረገድ ቀጣይነት ያለው ስራ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። አፋር ሳምንቱ በአፋር ክልል በማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ ያሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ወጣቶች፣ ባህልና ስፖርት ቢሮ ያስታወቀበትም ነበር። የአፋር ክልል አብዛኛው ማህበረሰብ ከፊል አርብቶ አደርና አርብቶ አደር በመሆኑ፣ በየዓመቱ የሚከናወኑ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክፍተቶች ለመሙላት ትልቅ ሚና አላቸው። በተለይም የአየር ንብረት መለዋወጥ፣ የውሃ እጥረት እና አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎችን ተቋቁሞ ዘላቂ ልማት ለማምጣት የወጣቶችና የህብረተሰቡ የተቀናጀ አቅም ወሳኝ ግብዓት ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። ማጠቃለያ ሳምንቱ በሁሉም ክልሎች መደበኛ የልማት፣ የማህበራዊ እና የሰላም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው የቀጠሉበትም ነበር። በሁሉም ክልሎች የስድስተኛ እና ስምንተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተካሄዷል። በተመሳሳይ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ዝግጅት በሁሉም ክልሎች እየተከናወነ ይገኛል።
ትንታኔዎች
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 1671
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 3799
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ። ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…!
Jun 15, 2026 2220
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 7558
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 3113
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 16849
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 9922
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 15682
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
የሀዋሳ ቀጣይ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ
Jun 24, 2026 464
ሀዋሳ፤ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ቀጣይ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ በእንዳለ ደበላ (ሀዋሳ ኢዜአ) ታቦር ተራራን በአንድ ጎኗ አላሙራ ተራራን ደግሞ በሌላው ጎኗ ታቅፋ የከተመችው ሀዋሳ ከተማ የፍቅር ሐይቅን ጨምሮ የተለያዩ የመስህብ ስፍራዎችንም በጉያዋ አቅፋ ይዛለች። ለባህላዊ ሕክምና አገልግሎት ጭምር የሚውሉት የወንዶገነት እና የይርጋለም የተፈጥሮ ፍል ውሀዎች ከሀዋሳ በቅርብ ርቀት ላይ መገኘታቸው ከተማዋ የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን በማድረግ በኩል የራሳቸው አስተዋጽኦ አላቸው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መዲናዋ ሀዋሳ ካሏት ተፈጥሯዊ የመስህብ ስፍራዎች በተጨማሪ የተለያዩ ባህላዊና ሀይማኖታዊ በዓላት በድምቀት የሚከበሩባት መሆኑም በጎብኚዎች ተመራጭ አድርጓታል። ሀዋሳ ባላት የተፈጥሮ ሀብት ላይ ተጨማሪ ውበትን ያላበሳት የኮሪደር ልማትም ከተማዋን ለኑሮ፣ ለሥራና ለኢንቨስትመንት ይበልጥ ምቹና ተመራጭ እያደረጋት ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወደከተማዋ የሚመጡ ጎብኚዎች ቁጥር እንዲበራከትና የቆይታ ጊዜያቸውንም እንዲያራዝሙ በማድረግ በኩል የኮሪደር ልማቱ አዎንታዊ ሚና መጫወት ጀምሯል። በከተማዋ ከሪፈራል ሰርክል እስከ መንቦ፣ ከሳውዝ ስፕሪንግ እስከ ፍቅር ሐይቅ፣ ከፍቅር ሐይቅ እስከ ሳውዝ ስታር ሆቴል የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች በተፈጥሮ የታደለችውን ሀዋሳን የበለጠ አድምቋታል። ውበቷን አጉልቶ ከማውጣት በተጨማሪ የከተማዋ ገቢ በማሳደግ በኩልም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው። የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን ምክትል ሀላፊና የደንበኞች አገልግሎት የታክሰ አሰባሰብ ዘርፍ ሀላፊ ወይዘሮ ሙላት ዮሴፍ በእዚህ ሀሳብ ይስማማሉ። እሳቸው እንዳሉት ባለፉት 11 ወራት በከተማዋ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል። አምና በተመሳሳይ ወቅት 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ እንደተሰበሰበ አስታውሰው የዘንድሮው 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ብልጫ አለው ብለዋል። ለገቢው መጨመር በምክንያትነት ከጠቀሷቸው አንዱ የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ የንግድ እንቅስቃሴውና የጎብኚው ቁጥር እያደገ መምጣት ነው። ይህን የከተማዋን የገቢ አቅም የበለጠ ለማሳደግ ያስችላል የተባለለት ተጨማሪ የኮሪደር ልማትም በአሁኑ ወቅት ሥራው ተጀምሯል። ከሳውዝ ስታር ሆቴል በቀድሞው መናኸሪያ እስከ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ አንዱ ሲሆን በፍጥነት ለማጠናቀቅም ታቅዶ እየተሰራ ነው። ሀዋሳ የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነቷልን ይበልጥ ለማሳደግ አሁንም በትጋት እየሰራች ነው፤ አሁንም ልማት ላይ ነች። ከከተማዋ መግቢያ የሐይቅ ዳርቻ ጀምሮ እስከ ታቦር ተራራ ድረስ 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የሐይቅ ዳርቻ ልማት ተጀምሯል። ይህም የከተማዋን እድገት ከማስቀጠል ባለፈ ይበልጥ የሚያደምቃት ነው። ተመራጭነቷነም ከፍ ያደርገዋል። በስድስት ወራት ውስጥ እንዲጠናቀቅ ታቅዶ ወደሥራ የተገባው የሐይቅ ዳርቻ የኮሪደር ልማት በመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራ የፍቅር ሐይቅ መግቢያ፣ አሞራ ገደል እና አሣ ገበያ አካባቢዎችን አካቶ የሚገነባ ነው። የሐይቅ ዳርቻ ልማቱ 60 ሜትር ወደ ሐይቁ ተገብቶ የሚከናወን ሲሆን ሰው ሰራሽ የውሀ ፏፏቴ፣ በሐይቁ ዳርቻ የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የተለያዩ ሱቆች፣ ሬስቶራንት፣ የመመልከቻ ማማዎች እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎችን አካቶ የሚሰራ ነው። ልማቱ ተጠናቆ ወደአገልግሎት ሲገባ በከተማዋ የቱሪዝም እንቅስቃሴ ላይ አዎንታዊ አበርክቶ ይኖረዋል። የከተማዋ የቱሪዝም መረጃ እንደሚያሳየው ካለፉት ዓመታት ወዲህ በሀዋሳ ከተማ የቱሪስት ፍሰት እየጨመረ መጥቷል። በተለይ በኮንፈረንስ ቱሪዝም ረገድ እና በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በኩል እየታየ ያለው ለውጥ ከተማዋን በቱሪስቶች ይበልጥ ተመራጭ አድርጓታል። ሀዋሳ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ጨምሮ የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮችን ለማስተናገድ ተመራጭ መሆኗ በስፖርት ቱሪዝም ዘርፍ ይበልጥ እንድትታወቅ እያደረገ ነው። ክለባቸውን ለመደገፍ ወደከተማዋ የሚመጡ ደጋፊዎች ዘርፉ እንዲነቃቃ የራሳቸውን አሻራም እያሳረፉ ይገኛሉ። በሀዋሳ ከተማ የሚከበሩ ሀይማኖታዊና ባህላዊ በዓላትም ከተማዋ በርካታ እንግዶችን እንድታስተናግድ ከማድረጋቸው ባለፈ ለከተማዋ ገቢ መጨመር የራሳቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የዓለም ቅርስ ሆኖ የተመዘገበው የሲዳማ ዘመን መለወጫ በዓል (ፊቼ ጨምበላላ) ለእዚህ ጥሩ ምሳሌ ነው። የጎብኚዎችን ቀልብ የሚስበው ይሄ በዓል ሌላው የሀዋሳ ከተማ ድምቀት ነው። በየዓመቱ በፍቼ ጨምባላላ በዓል ላይ ለመታደም ከሀገር ውስጥና ከመላው ዓለም በርካቶች ወደሀዋሳ ከተማ ስለሚመጡ ዋነኛው የቱሪስት መስህብ ነው ማለት ይቻላል። እነዚህ ባህላዊ፣ ሀይማኖታዊና ተፈጥሯዊ እሴቶችን በአግባቡ በማልማትና በማጎልበት ሀዋሳን ይበልጥ የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በቅርቡ የግንባታ ሥራው የተጀመረው የሀዋሳ ፍቅር ሐይቅ ዳርቻ ልማት ለእዚህ አንድ ማሳያ ነው። ልማቱ ከተማዋን የሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ብሎም የዓለም ኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ትልቅ ራዕይ ይዞ የተጀመረ ነው። ይህን የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ የኮሪደር ልማት በይፋ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ናቸው። የፍቅርና የሕብር ተምሳሌት የሆነችውን ሀዋሳ ውበቷን ይበልጥ ለማውጣትና ተመራጭ ለማድረግ የክልሉ መንግስት አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። እንደእሳቸው ገለጻ የኮሪደር ልማት ሥራው በፍጥነት እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይም ከሀዋሳ ሐይቅ እስከ ሞኖፖል ድረስ ያለውን አካባቢ በአምስተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ለማልማት ታቅዷል። ሀዋሳን የኮንፈረንስ፣ የስፖርትና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ትልቅ ዕድል ይዞ ለሚመጣው የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ተናግረዋል። የሀዋሳ ከተማን በሀገር ውስጥና በአፍሪካ ተመራጭ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ እንደሚሰራ የገለጹት ደግሞ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ ናቸው። ከተማዋን ይበለጥ ተመራጭ ለማድረግ ለሚከናወነው የመጀመሪያ ዙር የሐይቅ ዳርቻ ልማት 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል። ከዚህ ውስጥ ደግሞ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን የሚሆው ከማህበረሰቡ የሚሰበሰብ መሆኑን ነው ከንቲባው የገለጹት። ህዝቡም የከተማዋን ልማት ለመደገፍ የአቅሙን እያገዘ ነው። ለልማቱ በአይነት፣ በገንዘብና በዕውቀት እያደረገ ያለው ድጋፍ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ከ1 ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጠር ያነሱት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሀዋሳ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ቸርነት ፍላቴ ናቸው። በሀዋሳ በተለያዩ ምዕራፎች የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እስካሁን ከ2ሺህ ለሚበልጡ ሰዎቸ የሥራ ዕድል በመፍጠር ለበርካቶች ተጨማሪ ጥቅምን አስገኝቷል። የልማት ሥራዎች ለከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ሀዋሳን ውብ፣ ምቹና ለኑሮ ተመራጭ ከተማ እያደረጓት በመሆኑ በቀጣይም ህብረተሰቡን በማሳተፍ ልማቱ እንደሚጠናከር ነው የገለጹት። ከታቦርና አላሙራ ተራሮች እግር ሥር የከተመችው ሀዋሳ ዛሬም በሥራ ላይ ናት፣ የሚሰሩ ልጇቿ ዛሬም ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ከተማዋን ይብልጥ ከፍ ለማድረግ እየታተሩ ነው። የከተማዋን የቀጣይ የዕድገትና የውበት ምዕራፏን እውን ለማድረግ ልጆቿ በአቅማቸው አሻራቸውን ለማሳረፍ ወደተግባራዊ ሥራ ገብተዋል። በማማዋ ላይ ከፍ ብላ ጎልታ እንድትታይ የሚያደርጉት ርብርብ በዚህ ከቀጠለ ራዕዩዋን በማሳካት ሀዋሳን ከሀገር ውስጥ ባለፈ የአፍሪካ ኮንፈረንስ ማዕከል የማድረግ ግብ መሳካቱ አይቀሬ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት
Jun 23, 2026 1146
በዮሐንስ ደርበው ከሰብል ልማት አኳያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን ያደረገው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ አሁን ዘርፈ-ብዙ ጥቅሙ በተጨባጭ እየተገለጠ ነው። ከበርካታ ትሩፋቶቹ መካከልም የምርታማነት ማደግ ተጠቃሽ ነው።ይህን ተከትሎም የሕብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አድጓል። ይህን ሐሳብ በአኃዝ አስደግፎ ለማየት ያህል፤ ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፊት (በ2010 ዓ.ም) በሔክታር የሚመረተው ስንዴ 22 ኩንታል፣በቆሎ 30 ኩንታል፣ ጤፍ 17 ኩንታል እንዲሁም ገብስ 23 ኩንታል ነበር። ከኢንሼቲቩ ትግበራ በኋላ ደግሞ (በ2017 ዓ.ም) ስንዴ በሔክታር 36 ኩንታል፣ በቆሎ 46 ኩንታል፣ ጤፍ 20 ኩንታል፣ ገብስ 30 ኩንታል ማምረት ተችሏል። በዚህም መሠረት በ2017 ዓ.ም 7 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር መሬት በስንዴ ሰብል በመሸፈን 280 ሚሊየን ኩንታል ማምረት ተችሏል። ስንዴን በትጋት በማምረትም ከውጭ ለማስገባት ይወጣ የነበረን 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል። በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ ከፍራፍሬ አኳያ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፍራፍሬው ዘርፍ ዕድገትም ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል። በዚህም ገበያውን ከማረጋጋት ባለፈ ሕብረተሰቡ (አምራቹ) ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ በዚያው ልክ እንዲያድግ አስችሏል። ኢትዮጵያም በአፍሪካ አቮካዶን በቀዳሚነት ወደ ውጭ የምትልክ ሁለተኛዋ ሀገር እንድትሆን አስችሏታል። ከቡና ልማት መስፋፋት አኳያ ሌላኛው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በረከት የቡና ልማት መስፋፋትና የውጭ ምንዛሬ ማደግ ነው። ይህን በአሥረጂ አስደግፈን ብንመለከት፤ በ2011 ዓ.ም በ600 ሺህ ሔክታር ላይ ቡና ተተክሏል። 500 ሺህ ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል።738 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኝቷል። እንዲሁም በ2017 ዓ.ም 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ቡና ተተክሏል። 1 ነጥብ 58 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል። 2 ነጥብ 65 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ማግኘት ተችሏል። ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያ ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ጋር በተያያዘ ለ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል። ከላይ የተጠቀሱ ማሳያዎችን (ናሙናዎችን) ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በቀጥታ ለሕዝቡ ጥቅም የቆመ መርሐ-ግብር መሆኑን መገንዘብ አያዳግትም። ስለዚህ በቀጣይ ሕብረተሰቡ በዚህ ኢኒሼቲቭ ላይ ያለጠባቂነት በንቃት በመሳተፍ እና ባሕሉ በማድረግ ተጠቃሚነቱንም በዚያው ልክ ለማሳደግ መትጋት ይጠበቅበታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በቢሾፍቱ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ባለፉት ዓመታት 48 ቢሊየን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፤ በዘንድሮው መርሐ-ግብር ደግሞ 8 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተቀምጧል። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #ተስፋን_እንትከል