ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀቀ
Apr 26, 2026 63
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 18/2018(ኢዜአ)፦በተጠባቂው የወንዶች የለንደን ማራቶን ውድድር በለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል። በ46ኛው የለንደን ማራቶን የወንዶች ምድብ ውድድር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ውድድሩን 1:59.41 በመግባት ሁለተኛ ወጥቷል። ኬንያዊው አትሌት ሴባስቲያን ሳው ውድድሩን በበላይነት ሲያጠናቅቅ ዩጋንዳዊው ጃኮፕ ኪፕሊሞ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በሴቶች የለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ትዕግስት አሰፋ አሸነፈች
Apr 26, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 18/2018(ኢዜአ)፦ በተጠባቂው የሴቶች ለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ትዕግስት አሰፋ አሸንፋለች። በ46ኛውን የለንደን ማራቶን የሴቶች ምድብ ውድድር የፓሪስ ኦሎምፒክ የብር ሜዳልያ ባለቤቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ በበላይነት አሸንፋለች። አትሌት ትዕግስት አሰፋ ውድድሩን 2:15፡41 በሆነ ሠዓት በመግባት ነው ውድድሩን በበላይነት ጣጠናቀቀችው። በዚሁ ውድድር ኬንያውያኑ አትሌቶች ሐለን ኦቢሪ ሁለተኛ እንዲሁም ጆይሲሊን ጄፕኮስጊ ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ሪፎርም ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን በመፍጠር የውጭ ኩባንያዎችን ቀልብ እየሳበ ነው
Apr 26, 2026 54
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ ያደረገችው ሁሉን አቀፍ ሪፎርም ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን በመፍጠር የውጭ ኩባንያዎችን ቀልብ እየሳበ መሆኑን በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት የንግድ ምክር ቤት ገለጸ፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ባከናወነችው የሀገር በቀል ኢኮኖሚና በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሞች በርካታ ለውጦችን አስመዝግባለች፡፡ ግብርና፣ ማዕድን፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝምና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አድርጎ በመስራት ኢትዮጵያ ጸጋዋን እንድትጠቀም በር ከፍቶላታል፡፡ ኢትዮጵያ ያደረገችውን ሁሉን አቀፍ ሪፎርምን ተከትሎ የዓለም የኢንቨስትመንት የትኩረት ማዕከል ሆናለች፡፡ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት የንግድ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ባህሩ ተመስገን ለኢዜአ እንዳሉት፤ የንግድ ምክር ቤቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ከ200 በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎችን በአባልነት የያዘ ነው፡፡ ምክር ቤቱ አንጋፋና አዳዲስ የሚገቡ ኩባንያዎችን በሥሩ በመያዝ በተሰማሩበት ዘርፍ የሚገኝባቸውን የፋይናንስና የሰው ሀይል ችግር ከመንግሥት ጋር በመሆን እየፈታ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት የንግድ ምክር ቤት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በመተባበር አዳዲስ ኢንቨስተሮች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ በቅንጅት መሥራት የሚያስችል /Ethiopian Investment Deal Book/ አሳተመን ወደ ሥራ ገብተናል ብለዋል፡፡ በዚህም በኢትዮጵያና የአውሮፓ ህብረት ቢዝነስ ፎረም ከ100 በላይ ዓለም አቀፍ የአውሮፓ ኩባንያዎች የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጮች ለማየት መምጣታቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚስቡ በርካታ ሪፎርሞች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ ሪፎርሙ የዓለም አቀፍ ኢንቨስተሮችን ቀልብ እየሳበ ነው ብለዋል፡፡ የንግድ ምክር ቤቱ ነባር አባላትን መከታተል ብቻ ሳይሆን አዳዲስ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ እንዲሰማሩ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወሳኝ የፖሊሲ እርምጃዎችን እና ግልጽ አሰራሮችን በመዘርጋት ለኢንቨስትመንት ምቹ ከባቢ መፍጠሯን ገልጸው፤መንግሥት ለግሉ ዘርፍ በሰጠው ትኩረት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ያለባቸው ጊዜ ነው ብለዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
ታላቁ ሩጫ ኢትዮጵያን በማስተዋወቅ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው
Apr 26, 2026 62
ጅማ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ) የቱሪዝም ሚኒስቴር ታላቁ ሩጫ ኢትዮጵያን በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገለጸ። ዛሬ በጅማ ከተማ "ፖሊዮን በጋራ እናጥፋ" በሚል መሪ ሐሳብ የ15 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ተካሂዷል። በውድድሩ ላይ ከ10 ሀገራት የተውጣጡ እና ቁጥራቸው ከ4 ሺህ በላይ ተወዳዳሪዎች ተሳትፈዋል። የቱሪዝም ሚኒስቴር ተወካይ ተሾመ ተክሉ በዚሁ ወቅት፤ ታላቁ ሩጫ ኢትዮጵያን በማስተዋወቅ ትልቅ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። በየዓመቱ የተሳታፊዎች ቁጥር ከፍ እያለ መምጣቱን ጠቅሰው፤ በክልል ከተሞች መካሄዱ ከተሞቻችንን ለማስተዋወቀ ያግዛል ብለዋል። የፖሊዮ በሽታ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት የሚያስከትል አደገኛ በሽታ መሆኑን የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ተወካይ ደግሰው ደርሶ በበኩላቸው፤ የሚታየውን የግንዛቤ እጥረት ለመቅረፍና የክትባት ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በውድድሩ የጤና ተሳታፊዎች ፖሊዮን የማጥፋት መልዕክት በሩጫው ላይ አስተላልፈዋል። የኢትዮቴሌኮም ደቡብ ምዕራብ ሪጅናል ዳይሬክተር ክፍሌ ካሳ ስፖርት ትውልድን በመገንባት ሂደት ውስጥ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፤ ተቋማቸው እንደዚህ ያሉ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮግራሞችን በመደገፍ በጋራ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ውድድሩን በወንዶች ጃፈር ጀማል እንዲሁም በሴቶች የግሌ እሸቱ ያሸነፉ ሲሆን፤ የሜዳሊያና ሌሎች ሽልማቶችም ተበርክቶላቸዋል።
እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ናቸው
Apr 26, 2026 135
አሶሳ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በለውጡ መንግሥት እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት መሆናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ከዳር እስከ መሃል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የልማት ትንሳኤ" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አስር ኢብራሂም በዚሁ ወቅት፤ የለውጡ መንግሥት ብዝኀ የኢኮኖሚ ዘርፍን በመከተል ሀገሪቱ ጠንካራ የኢኮኖሚ መሠረት እንዲኖራት በትኩረት መሥራቱን ተናግረዋል። ለአብነትም የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያው የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲነቃቃ እና በዘርፉ የዜጎች ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት እንዲጨምር ማድረጉን አንስተዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም በሪፎርሙ በመታገዝና ያለውን የተፈጥሮ ጸጋ በመለየት እያደረጋቸው ያሉ የልማት እንቅስቃሴዎች እመርታዊ ውጤት እየተመዘገበባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ ሰላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ቢኒያም መንገሻ በበኩላቸው፤ የለውጡ መንግሥት አዳዲስ እሳቤዎችን በመተግበር እያከናወናቸው የሚገኙ የልማት፣ የፀጥታና የመልካም አሥተዳደር ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆኑን ጠቁመዋል። ለውጡን ተከትሎም ክልሉ ያስመዘገበው የመልማት ዕድል በኢኮኖሚው፣ በማኅበራዊውና በፖለቲካው መስኮች ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ማስቻሉን ተናግረዋል። ሀገራዊ ለውጡ በክልሉ ያስገኘውን የመሠረተ-ልማት፣ የሰላም እና የመልካም አሥተዳደር ሥራዎች ሕብረተሰቡን በማሳተፍ ቀጣይነት እንዲኖራቸው ማድረግ ይገባል ያሉት ደግሞ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ዚያድ አብዱላሂ ናቸው። እንደ ሀገር እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሆኑ እና የዜጎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ መሆናቸውን ነው አመራሮቹ የገለጹት።
ፖለቲካ
የለውጡ መንግሥት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት አረጋግጧል
Apr 26, 2026 275
አሶሳ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግሥት የክልሉን የመልማት ዐቅም በማሳደግ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት አረጋግጧል ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሠ መሥተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ከዳር እስከ መሃል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የልማት ትንሳኤ" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። ርዕሠ መሥተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የለውጡ መንግሥት የክልሉን የመልማት ዐቅም በማሳደግ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ አድርጓል። ከለውጡ በፊት ክልሉ የዳር ተመልካች በመሆኑ የመሠረተ-ልማት እጦት እና ኢፍትሐዊ የሀብት አጠቃቀም በመኖሩ የመልማት ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር አስታውሰዋል። ከለውጡ መንግሥት በኋላ በክልሉ አስተማማኝ ሰላም በመስፈኑ እና ፀጋዎቹን ለይቶ በማልማት ሕብረተሰቡ ከሀብቱ ተጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል። በማዕድን ዘርፍ የታየው ለውጥ የኢኮኖሚ መሠረት በመሆኑ በስፋት እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። የኮሪደር ልማት እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ውጤት መመዝገቡንም ገልጸዋል። ለውጡ የክልሉን የፖለቲካ ተሳትፎ ከማሳደግ ባለፈ የፖለቲካ ምኅዳሩን በማስፋት በሀገር ጉዳይ ላይ ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ጠቅሰዋል።
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በልዩ ሁኔታ እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየው ምዝገባ ማንን ይመለከታል?
Apr 26, 2026 261
1. የሀገር ውስጥ ተፈናቃዩች፣ 2. የዩኒቨርስቲ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች 3. በካምፕ የሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና በካምፕ የሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ቦርዱ ባቋቋማቸው ልዩ ምርጫ ጣቢያዎች የሚመዘገቡ ሲሆን፤ ለመመዝገብም • በአቅራቢያቸው በሚገኙ ቦርዱ ባቋቋማቸው ልዩ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መቅረብ • ማንነትን የሚያረጋግጥ ሠነድ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ደግሞ ቦርዱ ለተማሪዎቹ ባዘጋጀው ልዩ የመመዝገቢያ ድረ-ገጽ የሚመዘገቡ ሲሆን፤ ለመመዝገብም • ለምዝገባ በዩኒቨርስቲው ኔትዎርክ ላይ መሆን • ስልክ ወይም ኮምፒውተር (ላፕቶፕ/ ዴስክቶፕ) • ብሔራዊ መታወቂያ • ብሔራዊ መታወቂያ ሲያወጡ የወጣበት የስልክ ቁጥር የዩንቨርስቲ ተማሪዎች የድረ-ገጽ ላይ ምዝገባ ሂደት ቅደም ተከተል:- 1. በመራጭነት ለመመዝገብ የሚያስችለውን የመመዝገቢያ ድረ-ገጽ https://uni.mirchaye.nebe.org.et (በማንኛውም ብራውዘር በመጠቀም ማስገባት)፣ 2. ቀጥሎ በሚመጣላችሁ ገጽ ላይ ለእናንተ የሚስማማዎትን ቋንቋ ይመርጣሉ፣ 3. በመቀጠል “በፋይዳ አማካኝነት ወደ መለያ” የሚለውን ይጫናሉ፣ 4. የፋያዳ ገጾ ሲመጣ ከፋይዳ መታወቂያችሁ ላይ 16 አኅዝ ያለውን ቁጥር (FAN) ማስገባት እና ከፋይዳ በስልክዎ የሚላከውን ባለ ስድስት አኅዝ የአንድ ጊዜ የማረጋገጫ ቁጥር (OTP) ያስገባሉ፣ 5. ከፋይዳ ያገኛችሁት መረጃ ትክክል ከሆነ “ይቀጥሉ” የሚለውን በመጫን “መገለጫዎን ይጨርሱ” በሚለው ገጽ ውስጥ ስም፣ የአባት ስም፣ የአያት ስም በማስገባት በአካባቢው የሥራ ቋንቋ ይመዘግባሉ።የአካል ጉዳት ካለ ከዝርዝሩ በመምረጥ አፊዳቪት በመፈረም “ያስገቡ” የሚለውን በመጫን ቋሚ የመራጭነት መታወቂያዎን ያገኛሉ፤ ይህ መታወቂያ ቋሚ የመራጭነት መታወቂያዎ ሲሆን፤ መታወቂያዎን በስላክዎ አውርደው ወይም አትመው ሊይዙት ይገባል፣ 6. ቋሚ የመራጭነት መታወቂያ አገኙ ማለት ምዝገባዎ ተጠናቅቋል ማለት አይደለም፤ በመሆኑም “7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይመዝገቡ” የሚለውን ትጫናሉ፤ 7. በመቀጠል ድምፅ የምትሰጡበትን የምርጫ ጣቢያ ለማግኘት በመኖሪያ አድራሻዎ ወይም የሚገኙበትን ክልል፣ ዞን፣ ወረዳ፣ ቀበሌ ካለ ከሚመጣልዎ ዝርዝር ውስጥ ይመርጣሉ፣ 8. ከመረጡት ወረዳ ወይም ቀበሌ ሥር ከሚገኙ የምርጫ ጣቢያ ዝርዝር ውስጥ ለእርሶ የሚቀርቦትን ለማግኘት “ይፈልጉ” የሚለውን በመጫን በመረጡት አድራሻ ሥር የሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር ያገኛሉ፣ 9. በመቀጠል ካገኙት ዝርዝር ውስጥ ለእርሶ የሚቀርቦትን በመምረጥ በመረጡት ምርጫ ክልል በኗሪነት ያሎትን ቆይታ በዓመት እና በወር ያስገባሉ፣ 10. በመቀጠል ተማሪ መሆናችሁን የሚገልጸውን የተማሪ መታወቂያችሁን የፊት እና የጀርባ ገጽ ያያይዛሉ፣ 11. በመቀጠል ያስገቡትን መረጃ ትክክለኛነት የአፊዳቪት ሣጥን ውስጥ በመፈረም “ያረጋግጡ” የሚለውን በመጫን ለምርጫው ራሶትን ይመዘግባሉ፣ 12. በመቀጠል ለድምፅ መስጫ ቀን ይዘው የሚመጡትን ለአንድ ጊዜ የሚያገለግል የምርጫ ካርድ ከሲስተሙ ያገኛሉ። #ይመዝገቡ #ይሣተፉ
የአሥተዳደሩ የበጀት ዓመቱ 9 ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ መካሄድ ጀመረ
Apr 26, 2026 202
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፡-የከተማ አሥተዳደራችንን የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ሥራዎች አፈፃፀም ግምገማ መካሄድ ጀምሯል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላፉት መልዕክት፤ በበጀት ዓመቱ በእቅድ ከያዝናቸው ተግባራት 96 በመቶ መፈፀም ችለናል ብለዋል። ዛሬ የተጀመረው የግምገማ መድረክም ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ አመላክተዋል። በመድረኩም፤ በበጀት ዓመቱ ለመፈፀም ካቀድናቸው ውስጥ በዘጠኝ ወራት በጥብቅ ክትትል የተከናወኑትን የምንገመግምበት እና በቀሪ ወራት የትኩረት ማዕከል አድርገን የምንፈፅማቸው ጉዳዮች ይነሳሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት፤ በመልካም አሥተዳደር ተለይተው ያልተመለሱትን ምላሽ በመስጠት ማጠናቀቅ፣ የኑሮ ውድነትን የሚያባብሱ ችግሮችን በመቀነስ የዋጋ ንረትን መከላከል፣ የገበያ መዛባት ችግሮችን መከላከል፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግሥት አገልግሎት የጀመርነውን ውጤታማ ሥራ በቀሪ ወራት በተሟላ ሁኔታ በማጠናቀቅና ወደ ሥራ ማስገባት የሉትም በግምገማው እንደሚነሱ ጠቁመዋል። በተጨማሪም ቀሪ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ አድርጎ ወደ መሶብ ማስገባት፣ ተጀምረው በዚህ ዓመት መጠናቀቅ ያለባቸውን ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት ማጠናቀቅ የአፈፃፀም ግምገማ ማዕከላችን ይሆናሉ ብለዋል። ባለፋት አምስት ዓመታት የእቅድ አፈፃፀማችን ከ90 በመቶ በላይ እያደገ መጥቶ በ2018 ደግሞ 96 በመቶ የደረሰበት ውጤታማ አፈፃፀም መኖሩን በመገምገም፤ ይህንን እያደገ የመጣ የመፈፀም ልምድ አጠናክረን መቀጠል እንድንችል በትኩረት እንገመግማለን ሲሉም አስታውቀዋል። በተጨማሪም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ነፃ፣ ተዓማኒና ገለልተኛ ሆኖ እንዲከናወን ሁሉም አመራራችን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ትልቅ ኃላፊነት መወጣት እንዲችል የግምገማ አቅጣጫን አስቀምጠናል ነው ያሉት። የነበሩ ጥንካሬዎችን ማስቀጠል፣ ጉድለቶችን በመሙላት በቀሪዎች ወራት በላቀ መፈፀም የግምገማችን ማዕከል ይሆናል ብለዋል።
የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ ነው
Apr 25, 2026 1280
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ መሆኑን የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ገለጹ። የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት "የምርጫ ፍትህ በኢትዮጵያ የዳኝነት፣ የፍትሕና የአስተዳደር አካላት ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ የምርምር ኮንፈረንስ አካሂዷል። በዚሁ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ፤ የሕግ ሙያተኞችንና የህብረተሰቡን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የአውደ ጥናት መድረኮች በየጊዜው እንደሚዘጋጁ ገልጸዋል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዳኝነትና የአስተዳደር አካላት የምክክር መድረክም ሂደቱን ፍትሐዊና ሰላማዊ ለማድረግ ተጨማሪ አቅም መሆኑን ተናግረዋል። የምርጫ ዴሞክራሲያዊነትን ለማስጠበቅም የፖሊስ፣ ዓቃቤ ሕግና የፍትሕ ተቋማት ተመጋጋቢ የትብብር ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል። የዜጎች የድምፅ መስጫ ወረቀት ቅቡልነት ያለው መንግስት መመስረቻ ሕጋዊ ኃይል መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሐዊና ቅቡልነት ለማረጋገጥም ህብረተሰቡ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ተቋማት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥራ አመራር አባል አቶ ተክሊት ይመስል፤ በሕገ-መንግስቱና በአዋጅ በተሰጡ ተግባርና ኃላፊነቶች መሠረት የምርጫ ሂደቱ በገለልተኝነት እየተመራ ነው ብለዋል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ለመቋጨትም የሕግና የፍትሕ ተቋማት፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ዜጎችና ባለድርሻ አካላት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ በበኩላቸው ፤ ፖሊስ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝብን ተሳትፎ በማጎልበት የምርጫ ሂደት ሰላማዊነትን የማስጠበቅ ሥራ በብቃት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ለዚህም የምርጫ ቁሳቁስ ደኅንነትን የማስጠበቅና የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከህዝብ ጋር ተከታታይ ውይይቶች እንደሚካሄዱ አስረድተዋል። ከፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ ምትኩ ማዳ ባቀረቡት ፅሁፍ፤ የምርጫ ሂደት ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ ለሕግና ሕገ-መንግስታዊ መርህ ተከባሪነት በትኩረት ይሰራል ብለዋል። ለዚህም በምርጫ ሂደት ተዋናዮች ዘንድ ሊቀርቡ የሚችሉ የሕግና ይግባኝ አቤቱታዎችን አፋጣኝ መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አረጋግጠዋል። በፍትሕ ሚኒስቴር ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ጠገነኝ ትርፌ ባቀረቡት ጽሁፍ፤ ማንኛውም አካል ሕገ-መንግሥቱን የማስከበርና ለሕገ-መንግሥቱ ተገዢ የመሆን ኃላፊነት አለበት ብለዋል። የፍትሕ ሚኒስቴርም ለምርጫ ዓላማ ብቻ ምርመራና ክስ ላይ ለሚሰሩ ዓቃቢያነ ሕግ ስልጠና በመስጠት ግብረ ኃይልና ቡድኖችን በማዋቀር ወደሥራ ማስገባቱን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉትን የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን ሸኝተናል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Apr 25, 2026 1444
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉትን የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን ሸኝተናል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የፕሬዝደንቱ የኢትዮጵያ ቆይታ በሁለትዮሽ የጋራ አጀንዳዎች ላይ ውይይት የተካሄደበት እና በተለያዩ ዘርፎች ስምምነት የተደረሰበት ፍሬያማ ቆይታ ነበር ብለዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ ዋናውን ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻው ዝግጅት እየተከናወነ ይገኛል
Apr 25, 2026 976
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክሩ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተጠናቅቆ ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻው ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። በኢትዮጵያ ለዘመናት ሲንከባለሉ የቆዩ የልዩነት ሀሳቦችን በምክክር ለመፍታትና በሃሳብ የበላይነት የሚያምን ትውልድ ለመፍጠር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አዲስ ምዕራፍ ጀምሯል፡፡ ኮሚሽኑ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራን ያከናወነ ሲሆን ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን የመለየት ሥራ በስኬት አጠናቅቋል። ኮሚሽኑ የተሳታፊዎች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት፣ ከወረዳ ጀምሮ እስከ ክልሎችና ማዕከል ድረስ በግልጸኝነት የተካሄደ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ በዚህም ኮሚሽኑ ወደ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ምዕራፍ ለመሸጋገር የሚያስችለውን አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። ኮሚሽኑ እስካሁን ያከናወናቸው ተግባራት፣ ኢትዮጵያዊያን በውስጣዊ ጉዳዮቻቸው ላይ በነጻነት መክረው ዘላቂ ሰላምና ብሔራዊ መግባባት እንዲሰፍን የሚያስችል ታሪካዊ ዕድል የፈጠሩ መሆናቸው ይታመናል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለዘላቂ ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሰረት የሚጥል ነው፡፡ ምክክሩ ዜጎች በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች መግባባት ላይ በመድረስ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ዘላቂ ልማትና ዕድገት ማስመዝገብ የሚችሉበትን ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ የሀሳብ ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ በንግግር መፍታት ወሳኝ ነው ያሉት ዋና ኮሚሽነሩ፤ ዜጎች በሀገራዊ ምክክሩ የተፈጠረውን ዕድል በመጠቀም ለሀገራቸው ሰላምና ልማት ገንቢ ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በምክክር ሂደቱ በክልላቸውና በሀገራቸው ያሉ ችግሮችን ነቅሰው በማውጣት ለኮሚሽኑ ማቅረባቸውን አስታውሰዋል፡፡ በሁሉም ክልሎች፣ በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር መካሄዱንም ጠቅሰዋል፡፡ በቀጣይ ሳምንታት በሀገር አቀፍ ደረጃ 170 ለሚደርሱ የተመረጡ አማካሪዎች ስልጠና እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡ በሀገራዊ ምክክሩ ጉባኤ የሚሳተፉ ዜጎች ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል የሚወክሉ መሆናቸውን በማንሳት፤ ዋና ጉባኤውን ለማካሄድም የመጨረሻ ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ፣ እንደ ሀገር በማያግባቡ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር ረገድ በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ ይታወቃል።
ችግሮችን በምክክር በመፍታት የጋራ ሀገርን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ሚናችንን እናጠናክራለን
Apr 25, 2026 715
ወልቂጤ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ችግሮችን በምክክር በመፍታት የጋራ ሀገርን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ሚናችንን እናጠናክራለን ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን ገለጹ። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) ፤ ሀገራዊ ምክክር ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ ዩኒቨርሲቲው ለሂደቱ ስኬታማነት ጥናታዊ ጽሁፎችን በማዘጋጀትና የውይይት መድረኮችን በማመቻቸት ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መፍትሄ መሆኑን በመጥቀስ፣ ሀገራዊ አንድነትን ለማምጣት ያለውን ፋይዳ ለማሳካት ዩኒቨርስቲው አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ ከበደ ገለታ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እያከናወነ ያለው ተግባር ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ቀዳሚው አማራጭ መሆኑን ገልጸዋል። ተነጋግሮ እና ተመካክሮ እልባት ላይ መድረስ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መረጋጋትን ያመጣል፤ ይህም በዜጎች መካከል የጋራ መተማመንን ይፈጥራል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም የኮሚሽኑ የሥራ ዘመን መራዘሙ ይበልጥ አሳታፊ እና የጠራ ሥራ ለማከናወን ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ በምክክር ምዕራፎቹ ስኬት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላው የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህር ኢንጂነር ቀነኒ ኤልያስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አለመግባባቶችን በውይይት የመፍታት ባህል እንዲዳብር ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን የምክክሩን ስኬታማነት የሚያግዙ ጥረቶችን እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ለምክክሩ ሂደት ስኬታማነት ህዝቡ የሚያደርግው በጎ አስተዋጽኦ ውጤት እንዲያመጣ በተለይ ደግሞ የዘርፉ ምሁራን ሚና ትልቅ ነው ብለዋል። የቆዩና የማያግባቡ ችግሮች ላይ በጋራ በመምከር ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር የሚደረገው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን የሁሉም ጥረት ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ መምህር ስለሺ ታመነ (ዶ/ር) ናቸው። ይህ ሂደት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማሳያ መሆኑን በመጥቀስ፣ በምርምር የተደገፈ ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የክልሉን ህዝብ የሰላምና የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራትን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል
Apr 25, 2026 568
ባህርዳር፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ የክልሉን ህዝብ የሰላም እና የልማት ተግባራት ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለፁ። ''አርቆ ማየት አልቆ መስራት'' በሚል መሪ ሃሳብ የክልሉ ያለፉት ዘጠኝ ወራት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ በባህር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በመድረኩ እንደገለፁት፤ በክልሉ የሚከናወኑ ሁሉም ተግባራት ከዚህ ቀደም ከነበረው የአሰራር ሂደት በተለየ ሁኔታ፣ በልዩ ትኩረትና በተሻለ መንገድ መፈፀም ይገባል። በተለይም በክልሉ ሰላምን በተቀናጀ አግባብ ከማስከበር ባሻገር ህዝብ በየደረጃው የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዘላቂነት የመፍታት ስራ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት። የክልሉን ህዝብ የሰላሙም ሆነ የልማቱ ግንባር ቀደም ተሳታፊና ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራትን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል ብለዋል። እንዲሁም ነባራዊ ሁኔታውን ታሳቢ በማድረግና በመረዳት አመራሩ ሁሉን አቀፍ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሔደው የግምገማ መድረክ የተገኙ ስኬቶችን ከማስቀጠል ባለፈ በአፈፃፀም ወቅት የታዩ እንከኖችን በጥልቀት በማየት በቀሪ ወራት በጊዜ የለኝም መንፈስ እንዲፈፀሙ የሚያደርግ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም አመላክተዋል። በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ በበኩላቸው፤ በክልሉ ባለፋት ወራት ዘላቂ ሰላምን መገንባት የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት በቅንጅት ተከናውነዋል ብለዋል። እንዲሁም ጠንካራ አመራር በመስጠት የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውንም አስረድተዋል። በየዘርፋ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በቀጣይ በላቀ ስኬት ማከናወን እንዲቻል አመራሩ በትኩረት ስራዎችን ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። በመድረኩ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች እየተሳተፉ ሲሆን የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎም ይጠበቃል።
ፖለቲካ
የለውጡ መንግሥት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት አረጋግጧል
Apr 26, 2026 275
አሶሳ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግሥት የክልሉን የመልማት ዐቅም በማሳደግ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት አረጋግጧል ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሠ መሥተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ከዳር እስከ መሃል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የልማት ትንሳኤ" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። ርዕሠ መሥተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የለውጡ መንግሥት የክልሉን የመልማት ዐቅም በማሳደግ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ አድርጓል። ከለውጡ በፊት ክልሉ የዳር ተመልካች በመሆኑ የመሠረተ-ልማት እጦት እና ኢፍትሐዊ የሀብት አጠቃቀም በመኖሩ የመልማት ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር አስታውሰዋል። ከለውጡ መንግሥት በኋላ በክልሉ አስተማማኝ ሰላም በመስፈኑ እና ፀጋዎቹን ለይቶ በማልማት ሕብረተሰቡ ከሀብቱ ተጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል። በማዕድን ዘርፍ የታየው ለውጥ የኢኮኖሚ መሠረት በመሆኑ በስፋት እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። የኮሪደር ልማት እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ውጤት መመዝገቡንም ገልጸዋል። ለውጡ የክልሉን የፖለቲካ ተሳትፎ ከማሳደግ ባለፈ የፖለቲካ ምኅዳሩን በማስፋት በሀገር ጉዳይ ላይ ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ጠቅሰዋል።
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በልዩ ሁኔታ እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየው ምዝገባ ማንን ይመለከታል?
Apr 26, 2026 261
1. የሀገር ውስጥ ተፈናቃዩች፣ 2. የዩኒቨርስቲ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች 3. በካምፕ የሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና በካምፕ የሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ቦርዱ ባቋቋማቸው ልዩ ምርጫ ጣቢያዎች የሚመዘገቡ ሲሆን፤ ለመመዝገብም • በአቅራቢያቸው በሚገኙ ቦርዱ ባቋቋማቸው ልዩ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መቅረብ • ማንነትን የሚያረጋግጥ ሠነድ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ደግሞ ቦርዱ ለተማሪዎቹ ባዘጋጀው ልዩ የመመዝገቢያ ድረ-ገጽ የሚመዘገቡ ሲሆን፤ ለመመዝገብም • ለምዝገባ በዩኒቨርስቲው ኔትዎርክ ላይ መሆን • ስልክ ወይም ኮምፒውተር (ላፕቶፕ/ ዴስክቶፕ) • ብሔራዊ መታወቂያ • ብሔራዊ መታወቂያ ሲያወጡ የወጣበት የስልክ ቁጥር የዩንቨርስቲ ተማሪዎች የድረ-ገጽ ላይ ምዝገባ ሂደት ቅደም ተከተል:- 1. በመራጭነት ለመመዝገብ የሚያስችለውን የመመዝገቢያ ድረ-ገጽ https://uni.mirchaye.nebe.org.et (በማንኛውም ብራውዘር በመጠቀም ማስገባት)፣ 2. ቀጥሎ በሚመጣላችሁ ገጽ ላይ ለእናንተ የሚስማማዎትን ቋንቋ ይመርጣሉ፣ 3. በመቀጠል “በፋይዳ አማካኝነት ወደ መለያ” የሚለውን ይጫናሉ፣ 4. የፋያዳ ገጾ ሲመጣ ከፋይዳ መታወቂያችሁ ላይ 16 አኅዝ ያለውን ቁጥር (FAN) ማስገባት እና ከፋይዳ በስልክዎ የሚላከውን ባለ ስድስት አኅዝ የአንድ ጊዜ የማረጋገጫ ቁጥር (OTP) ያስገባሉ፣ 5. ከፋይዳ ያገኛችሁት መረጃ ትክክል ከሆነ “ይቀጥሉ” የሚለውን በመጫን “መገለጫዎን ይጨርሱ” በሚለው ገጽ ውስጥ ስም፣ የአባት ስም፣ የአያት ስም በማስገባት በአካባቢው የሥራ ቋንቋ ይመዘግባሉ።የአካል ጉዳት ካለ ከዝርዝሩ በመምረጥ አፊዳቪት በመፈረም “ያስገቡ” የሚለውን በመጫን ቋሚ የመራጭነት መታወቂያዎን ያገኛሉ፤ ይህ መታወቂያ ቋሚ የመራጭነት መታወቂያዎ ሲሆን፤ መታወቂያዎን በስላክዎ አውርደው ወይም አትመው ሊይዙት ይገባል፣ 6. ቋሚ የመራጭነት መታወቂያ አገኙ ማለት ምዝገባዎ ተጠናቅቋል ማለት አይደለም፤ በመሆኑም “7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይመዝገቡ” የሚለውን ትጫናሉ፤ 7. በመቀጠል ድምፅ የምትሰጡበትን የምርጫ ጣቢያ ለማግኘት በመኖሪያ አድራሻዎ ወይም የሚገኙበትን ክልል፣ ዞን፣ ወረዳ፣ ቀበሌ ካለ ከሚመጣልዎ ዝርዝር ውስጥ ይመርጣሉ፣ 8. ከመረጡት ወረዳ ወይም ቀበሌ ሥር ከሚገኙ የምርጫ ጣቢያ ዝርዝር ውስጥ ለእርሶ የሚቀርቦትን ለማግኘት “ይፈልጉ” የሚለውን በመጫን በመረጡት አድራሻ ሥር የሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር ያገኛሉ፣ 9. በመቀጠል ካገኙት ዝርዝር ውስጥ ለእርሶ የሚቀርቦትን በመምረጥ በመረጡት ምርጫ ክልል በኗሪነት ያሎትን ቆይታ በዓመት እና በወር ያስገባሉ፣ 10. በመቀጠል ተማሪ መሆናችሁን የሚገልጸውን የተማሪ መታወቂያችሁን የፊት እና የጀርባ ገጽ ያያይዛሉ፣ 11. በመቀጠል ያስገቡትን መረጃ ትክክለኛነት የአፊዳቪት ሣጥን ውስጥ በመፈረም “ያረጋግጡ” የሚለውን በመጫን ለምርጫው ራሶትን ይመዘግባሉ፣ 12. በመቀጠል ለድምፅ መስጫ ቀን ይዘው የሚመጡትን ለአንድ ጊዜ የሚያገለግል የምርጫ ካርድ ከሲስተሙ ያገኛሉ። #ይመዝገቡ #ይሣተፉ
የአሥተዳደሩ የበጀት ዓመቱ 9 ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ መካሄድ ጀመረ
Apr 26, 2026 202
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፡-የከተማ አሥተዳደራችንን የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ሥራዎች አፈፃፀም ግምገማ መካሄድ ጀምሯል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላፉት መልዕክት፤ በበጀት ዓመቱ በእቅድ ከያዝናቸው ተግባራት 96 በመቶ መፈፀም ችለናል ብለዋል። ዛሬ የተጀመረው የግምገማ መድረክም ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ አመላክተዋል። በመድረኩም፤ በበጀት ዓመቱ ለመፈፀም ካቀድናቸው ውስጥ በዘጠኝ ወራት በጥብቅ ክትትል የተከናወኑትን የምንገመግምበት እና በቀሪ ወራት የትኩረት ማዕከል አድርገን የምንፈፅማቸው ጉዳዮች ይነሳሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት፤ በመልካም አሥተዳደር ተለይተው ያልተመለሱትን ምላሽ በመስጠት ማጠናቀቅ፣ የኑሮ ውድነትን የሚያባብሱ ችግሮችን በመቀነስ የዋጋ ንረትን መከላከል፣ የገበያ መዛባት ችግሮችን መከላከል፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግሥት አገልግሎት የጀመርነውን ውጤታማ ሥራ በቀሪ ወራት በተሟላ ሁኔታ በማጠናቀቅና ወደ ሥራ ማስገባት የሉትም በግምገማው እንደሚነሱ ጠቁመዋል። በተጨማሪም ቀሪ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ አድርጎ ወደ መሶብ ማስገባት፣ ተጀምረው በዚህ ዓመት መጠናቀቅ ያለባቸውን ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት ማጠናቀቅ የአፈፃፀም ግምገማ ማዕከላችን ይሆናሉ ብለዋል። ባለፋት አምስት ዓመታት የእቅድ አፈፃፀማችን ከ90 በመቶ በላይ እያደገ መጥቶ በ2018 ደግሞ 96 በመቶ የደረሰበት ውጤታማ አፈፃፀም መኖሩን በመገምገም፤ ይህንን እያደገ የመጣ የመፈፀም ልምድ አጠናክረን መቀጠል እንድንችል በትኩረት እንገመግማለን ሲሉም አስታውቀዋል። በተጨማሪም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ነፃ፣ ተዓማኒና ገለልተኛ ሆኖ እንዲከናወን ሁሉም አመራራችን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ትልቅ ኃላፊነት መወጣት እንዲችል የግምገማ አቅጣጫን አስቀምጠናል ነው ያሉት። የነበሩ ጥንካሬዎችን ማስቀጠል፣ ጉድለቶችን በመሙላት በቀሪዎች ወራት በላቀ መፈፀም የግምገማችን ማዕከል ይሆናል ብለዋል።
የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ ነው
Apr 25, 2026 1280
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ መሆኑን የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ገለጹ። የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት "የምርጫ ፍትህ በኢትዮጵያ የዳኝነት፣ የፍትሕና የአስተዳደር አካላት ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ የምርምር ኮንፈረንስ አካሂዷል። በዚሁ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ፤ የሕግ ሙያተኞችንና የህብረተሰቡን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የአውደ ጥናት መድረኮች በየጊዜው እንደሚዘጋጁ ገልጸዋል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዳኝነትና የአስተዳደር አካላት የምክክር መድረክም ሂደቱን ፍትሐዊና ሰላማዊ ለማድረግ ተጨማሪ አቅም መሆኑን ተናግረዋል። የምርጫ ዴሞክራሲያዊነትን ለማስጠበቅም የፖሊስ፣ ዓቃቤ ሕግና የፍትሕ ተቋማት ተመጋጋቢ የትብብር ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል። የዜጎች የድምፅ መስጫ ወረቀት ቅቡልነት ያለው መንግስት መመስረቻ ሕጋዊ ኃይል መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሐዊና ቅቡልነት ለማረጋገጥም ህብረተሰቡ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ተቋማት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥራ አመራር አባል አቶ ተክሊት ይመስል፤ በሕገ-መንግስቱና በአዋጅ በተሰጡ ተግባርና ኃላፊነቶች መሠረት የምርጫ ሂደቱ በገለልተኝነት እየተመራ ነው ብለዋል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ለመቋጨትም የሕግና የፍትሕ ተቋማት፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ዜጎችና ባለድርሻ አካላት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ በበኩላቸው ፤ ፖሊስ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝብን ተሳትፎ በማጎልበት የምርጫ ሂደት ሰላማዊነትን የማስጠበቅ ሥራ በብቃት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ለዚህም የምርጫ ቁሳቁስ ደኅንነትን የማስጠበቅና የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከህዝብ ጋር ተከታታይ ውይይቶች እንደሚካሄዱ አስረድተዋል። ከፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ ምትኩ ማዳ ባቀረቡት ፅሁፍ፤ የምርጫ ሂደት ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ ለሕግና ሕገ-መንግስታዊ መርህ ተከባሪነት በትኩረት ይሰራል ብለዋል። ለዚህም በምርጫ ሂደት ተዋናዮች ዘንድ ሊቀርቡ የሚችሉ የሕግና ይግባኝ አቤቱታዎችን አፋጣኝ መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አረጋግጠዋል። በፍትሕ ሚኒስቴር ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ጠገነኝ ትርፌ ባቀረቡት ጽሁፍ፤ ማንኛውም አካል ሕገ-መንግሥቱን የማስከበርና ለሕገ-መንግሥቱ ተገዢ የመሆን ኃላፊነት አለበት ብለዋል። የፍትሕ ሚኒስቴርም ለምርጫ ዓላማ ብቻ ምርመራና ክስ ላይ ለሚሰሩ ዓቃቢያነ ሕግ ስልጠና በመስጠት ግብረ ኃይልና ቡድኖችን በማዋቀር ወደሥራ ማስገባቱን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉትን የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን ሸኝተናል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Apr 25, 2026 1444
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉትን የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን ሸኝተናል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የፕሬዝደንቱ የኢትዮጵያ ቆይታ በሁለትዮሽ የጋራ አጀንዳዎች ላይ ውይይት የተካሄደበት እና በተለያዩ ዘርፎች ስምምነት የተደረሰበት ፍሬያማ ቆይታ ነበር ብለዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ ዋናውን ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻው ዝግጅት እየተከናወነ ይገኛል
Apr 25, 2026 976
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክሩ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተጠናቅቆ ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻው ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። በኢትዮጵያ ለዘመናት ሲንከባለሉ የቆዩ የልዩነት ሀሳቦችን በምክክር ለመፍታትና በሃሳብ የበላይነት የሚያምን ትውልድ ለመፍጠር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አዲስ ምዕራፍ ጀምሯል፡፡ ኮሚሽኑ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራን ያከናወነ ሲሆን ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን የመለየት ሥራ በስኬት አጠናቅቋል። ኮሚሽኑ የተሳታፊዎች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት፣ ከወረዳ ጀምሮ እስከ ክልሎችና ማዕከል ድረስ በግልጸኝነት የተካሄደ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ በዚህም ኮሚሽኑ ወደ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ምዕራፍ ለመሸጋገር የሚያስችለውን አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። ኮሚሽኑ እስካሁን ያከናወናቸው ተግባራት፣ ኢትዮጵያዊያን በውስጣዊ ጉዳዮቻቸው ላይ በነጻነት መክረው ዘላቂ ሰላምና ብሔራዊ መግባባት እንዲሰፍን የሚያስችል ታሪካዊ ዕድል የፈጠሩ መሆናቸው ይታመናል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለዘላቂ ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሰረት የሚጥል ነው፡፡ ምክክሩ ዜጎች በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች መግባባት ላይ በመድረስ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ዘላቂ ልማትና ዕድገት ማስመዝገብ የሚችሉበትን ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ የሀሳብ ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ በንግግር መፍታት ወሳኝ ነው ያሉት ዋና ኮሚሽነሩ፤ ዜጎች በሀገራዊ ምክክሩ የተፈጠረውን ዕድል በመጠቀም ለሀገራቸው ሰላምና ልማት ገንቢ ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በምክክር ሂደቱ በክልላቸውና በሀገራቸው ያሉ ችግሮችን ነቅሰው በማውጣት ለኮሚሽኑ ማቅረባቸውን አስታውሰዋል፡፡ በሁሉም ክልሎች፣ በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር መካሄዱንም ጠቅሰዋል፡፡ በቀጣይ ሳምንታት በሀገር አቀፍ ደረጃ 170 ለሚደርሱ የተመረጡ አማካሪዎች ስልጠና እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡ በሀገራዊ ምክክሩ ጉባኤ የሚሳተፉ ዜጎች ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል የሚወክሉ መሆናቸውን በማንሳት፤ ዋና ጉባኤውን ለማካሄድም የመጨረሻ ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ፣ እንደ ሀገር በማያግባቡ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር ረገድ በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ ይታወቃል።
ችግሮችን በምክክር በመፍታት የጋራ ሀገርን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ሚናችንን እናጠናክራለን
Apr 25, 2026 715
ወልቂጤ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ችግሮችን በምክክር በመፍታት የጋራ ሀገርን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ሚናችንን እናጠናክራለን ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን ገለጹ። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) ፤ ሀገራዊ ምክክር ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ ዩኒቨርሲቲው ለሂደቱ ስኬታማነት ጥናታዊ ጽሁፎችን በማዘጋጀትና የውይይት መድረኮችን በማመቻቸት ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መፍትሄ መሆኑን በመጥቀስ፣ ሀገራዊ አንድነትን ለማምጣት ያለውን ፋይዳ ለማሳካት ዩኒቨርስቲው አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ ከበደ ገለታ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እያከናወነ ያለው ተግባር ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ቀዳሚው አማራጭ መሆኑን ገልጸዋል። ተነጋግሮ እና ተመካክሮ እልባት ላይ መድረስ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መረጋጋትን ያመጣል፤ ይህም በዜጎች መካከል የጋራ መተማመንን ይፈጥራል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም የኮሚሽኑ የሥራ ዘመን መራዘሙ ይበልጥ አሳታፊ እና የጠራ ሥራ ለማከናወን ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ በምክክር ምዕራፎቹ ስኬት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላው የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህር ኢንጂነር ቀነኒ ኤልያስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አለመግባባቶችን በውይይት የመፍታት ባህል እንዲዳብር ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን የምክክሩን ስኬታማነት የሚያግዙ ጥረቶችን እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ለምክክሩ ሂደት ስኬታማነት ህዝቡ የሚያደርግው በጎ አስተዋጽኦ ውጤት እንዲያመጣ በተለይ ደግሞ የዘርፉ ምሁራን ሚና ትልቅ ነው ብለዋል። የቆዩና የማያግባቡ ችግሮች ላይ በጋራ በመምከር ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር የሚደረገው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን የሁሉም ጥረት ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ መምህር ስለሺ ታመነ (ዶ/ር) ናቸው። ይህ ሂደት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማሳያ መሆኑን በመጥቀስ፣ በምርምር የተደገፈ ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የክልሉን ህዝብ የሰላምና የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራትን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል
Apr 25, 2026 568
ባህርዳር፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ የክልሉን ህዝብ የሰላም እና የልማት ተግባራት ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለፁ። ''አርቆ ማየት አልቆ መስራት'' በሚል መሪ ሃሳብ የክልሉ ያለፉት ዘጠኝ ወራት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ በባህር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በመድረኩ እንደገለፁት፤ በክልሉ የሚከናወኑ ሁሉም ተግባራት ከዚህ ቀደም ከነበረው የአሰራር ሂደት በተለየ ሁኔታ፣ በልዩ ትኩረትና በተሻለ መንገድ መፈፀም ይገባል። በተለይም በክልሉ ሰላምን በተቀናጀ አግባብ ከማስከበር ባሻገር ህዝብ በየደረጃው የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዘላቂነት የመፍታት ስራ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት። የክልሉን ህዝብ የሰላሙም ሆነ የልማቱ ግንባር ቀደም ተሳታፊና ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራትን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል ብለዋል። እንዲሁም ነባራዊ ሁኔታውን ታሳቢ በማድረግና በመረዳት አመራሩ ሁሉን አቀፍ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሔደው የግምገማ መድረክ የተገኙ ስኬቶችን ከማስቀጠል ባለፈ በአፈፃፀም ወቅት የታዩ እንከኖችን በጥልቀት በማየት በቀሪ ወራት በጊዜ የለኝም መንፈስ እንዲፈፀሙ የሚያደርግ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም አመላክተዋል። በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ በበኩላቸው፤ በክልሉ ባለፋት ወራት ዘላቂ ሰላምን መገንባት የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት በቅንጅት ተከናውነዋል ብለዋል። እንዲሁም ጠንካራ አመራር በመስጠት የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውንም አስረድተዋል። በየዘርፋ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በቀጣይ በላቀ ስኬት ማከናወን እንዲቻል አመራሩ በትኩረት ስራዎችን ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። በመድረኩ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች እየተሳተፉ ሲሆን የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎም ይጠበቃል።
ማህበራዊ
እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ናቸው
Apr 26, 2026 135
አሶሳ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በለውጡ መንግሥት እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት መሆናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ከዳር እስከ መሃል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የልማት ትንሳኤ" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አስር ኢብራሂም በዚሁ ወቅት፤ የለውጡ መንግሥት ብዝኀ የኢኮኖሚ ዘርፍን በመከተል ሀገሪቱ ጠንካራ የኢኮኖሚ መሠረት እንዲኖራት በትኩረት መሥራቱን ተናግረዋል። ለአብነትም የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያው የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲነቃቃ እና በዘርፉ የዜጎች ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት እንዲጨምር ማድረጉን አንስተዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም በሪፎርሙ በመታገዝና ያለውን የተፈጥሮ ጸጋ በመለየት እያደረጋቸው ያሉ የልማት እንቅስቃሴዎች እመርታዊ ውጤት እየተመዘገበባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ ሰላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ቢኒያም መንገሻ በበኩላቸው፤ የለውጡ መንግሥት አዳዲስ እሳቤዎችን በመተግበር እያከናወናቸው የሚገኙ የልማት፣ የፀጥታና የመልካም አሥተዳደር ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆኑን ጠቁመዋል። ለውጡን ተከትሎም ክልሉ ያስመዘገበው የመልማት ዕድል በኢኮኖሚው፣ በማኅበራዊውና በፖለቲካው መስኮች ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ማስቻሉን ተናግረዋል። ሀገራዊ ለውጡ በክልሉ ያስገኘውን የመሠረተ-ልማት፣ የሰላም እና የመልካም አሥተዳደር ሥራዎች ሕብረተሰቡን በማሳተፍ ቀጣይነት እንዲኖራቸው ማድረግ ይገባል ያሉት ደግሞ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ዚያድ አብዱላሂ ናቸው። እንደ ሀገር እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሆኑ እና የዜጎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ መሆናቸውን ነው አመራሮቹ የገለጹት።
የወባ በሽታን ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Apr 26, 2026 72
ጎንደር፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በክረምት መግቢያ ሊከሰት የሚችልን የወባ በሽታ ለመከላከል የአጎበር ሥርጭትና የኬሚካል ርጭት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ጤና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ኃላፊ ምሳ ታረቀኝ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ 10 ወረዳዎች እና 207 ቀበሌዎች ለወባ በሽታ ተጋላጭ ናቸው። በዚህም መሠረት ሕብረተሰቡን ያሳተፈ የአካባቢ ቅኝትና ቁጥጥር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አረጋግጠዋል። በሽታውን ቀድሞ ለመከላከልም ከ100 ሺህ በላይ የወባ ትንኝ መከላከያ የአልጋ አጎበር እየተሠራጨ መሆኑን ገልጸው፤ ከ200 ሺህ በሚበልጡ መኖሪያ ቤቶች ላይም የኬሚካል ርጭት ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። በመኖሪያ ቤቶች የተደረገው የኬሚካል ርጭት ከ800 ሺህ በላይ ዜጎችን ከወባ በሽታ ለመጠበቅ እንደሚያስችልም ጠቁመዋል። የጤና ባለሙያዎችም በአልጋ አጎበር አጠቃቀምና በኬሚካል ርጭት ወቅት መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ ሕብረተሰቡን እያስገነዘቡ እንደሚገኙ አመላክተዋል። በማኅበረሰቡ ተሳትፎ "የአርብ ጠንካራ እጆች" በሚል መሪ ሐሳብ የወባ ትንኝ መራቢያ ስፍራዎችን የማጽዳትና የታቆረ ውኃን የማፋሰስ ተግባር መቀጠሉንም አስረድተዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የወባ ቁጥጥርና ሕክምና ተግባራት በወባ በሽታ የሚጠቁ ኅሙማን ቁጥር ከመቀነስ ባለፈ ሞትን ማስቀረት መቻሉንም አረጋግጠዋል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 151
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
የግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ለማዘመን ጉልህ ድርሻ እየተወጡ ነው
Apr 25, 2026 380
ሮቤ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የወጣቶችን የሥራ ፈጣሪነት ክህሎት ከማሳደግ ባሻገር የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ለማዘመን ጉልህ ድርሻ እየተወጡ መሆኑ ተመላከተ። የአጋርፋ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ በተለያዩ ሙያዎች በደረጃ 4 ያሰለጠናቸውን 592 ተማሪዎችን አስመርቋል። ተማሪዎቹ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ፣ በእጽዋት ሳይንስ፣ በእንስሳት ሳይንስ፣ በመሬት አስተዳደርና ልማት ዘርፍ የተመረቁ መሆናቸውም ተመልክቷል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) እንዳሉት በለውጡ ዓመታት የክህሎት ልማትንና የቴክኒክና ሙያ ዘርፍን ለማጠናከር በተሰሩ ሥራዎች አበረታች ለውጦች ታይተዋል። በዚህም ተግባራዊ የተደረጉ ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃዎች ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህል እንዲነቃቃ አስችሏል ብለዋል። በተለይ በግብርናው ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ የሚያሰለጥኑ የግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የወጣቶችን የሥራ ፈጣሪነት ክህሎት ከማሳደግ ባሻገር የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ለማዘመን ጉልህ ድርሻ እየተወጡ መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪም ዘመናዊ የመሬት አስተዳደር ልማትን ተደራሽ በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች እንዲፈቱ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥሩም አስረድተዋል። የአጋርፋ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅም የዚሁ አንዱ ማሳያና በዘርፉ የተማረ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ አይነተኛ ሚና እየተወጣ ያለ አንጋፋ ተቋም መሆኑንም አክለዋል። ተመራቂዎችም በኮሌጁ ቆይታቸው ያገኙትን የንድፈ ሀሳብ ዕውቀት በአካባቢያቸው ከሚገኙ ፀጋዎች ጋር በማቀናጀት በተማሩት ሙያ አርሶና አርብቶ አደሩን በቅንነት እንዲያገለግሉ አስገንዝበዋል። የአጋርፋ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ ዲን አቶ ፍራኦል ኢደኦ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኮሌጁ የግብርና ክፍለ ኢኮኖሚውን ለማዘመን በዘርፉ የተማረ የሰው ኃይል የማፍራት ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው። በተለይ በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በጥናትና ምርምር እንዲፈቱ ለማስቻል በዘርፉ የተመረቁ ሰልጣኞች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን አክለዋል። ኮሌጁ ከመማር ማስተማሩ ተግባር በተጓዳኝ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ምርምሮችና የማህበረሰብ አገልግሎቶችን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሬት አስተዳደርና ልማት ዘርፍ የተመረቀው ፉአድ ሲራጅ፤ በኮሌጁ የትምህርት ቆይታው ያገኘውን ዕውቀት ለማህበረሰብ አገልግሎት ለማዋል ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል። ተማሪ አቤል አዱኛ በበኩሉ፤ በተለይ በተፈጥሮ ሃብት ልማት ዘርፍ በአገሪቱ የተጀመሩ ውጤታማ ሥራዎች ይበልጥ እንዲጠናከሩ የበኩሌን እወጣለሁ ብሏል። በምረቃ መርሐግብሩ በትምህርታቸው ብልጫ ላስመዘገቡ ተማሪዎች የሜዳሊያና የዋንጫ ሽልማት በዕለቱ የክብር እንግዶች ተበርክቷል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ሪፎርም ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን በመፍጠር የውጭ ኩባንያዎችን ቀልብ እየሳበ ነው
Apr 26, 2026 54
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ ያደረገችው ሁሉን አቀፍ ሪፎርም ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን በመፍጠር የውጭ ኩባንያዎችን ቀልብ እየሳበ መሆኑን በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት የንግድ ምክር ቤት ገለጸ፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ባከናወነችው የሀገር በቀል ኢኮኖሚና በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሞች በርካታ ለውጦችን አስመዝግባለች፡፡ ግብርና፣ ማዕድን፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝምና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አድርጎ በመስራት ኢትዮጵያ ጸጋዋን እንድትጠቀም በር ከፍቶላታል፡፡ ኢትዮጵያ ያደረገችውን ሁሉን አቀፍ ሪፎርምን ተከትሎ የዓለም የኢንቨስትመንት የትኩረት ማዕከል ሆናለች፡፡ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት የንግድ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ባህሩ ተመስገን ለኢዜአ እንዳሉት፤ የንግድ ምክር ቤቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ከ200 በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎችን በአባልነት የያዘ ነው፡፡ ምክር ቤቱ አንጋፋና አዳዲስ የሚገቡ ኩባንያዎችን በሥሩ በመያዝ በተሰማሩበት ዘርፍ የሚገኝባቸውን የፋይናንስና የሰው ሀይል ችግር ከመንግሥት ጋር በመሆን እየፈታ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት የንግድ ምክር ቤት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በመተባበር አዳዲስ ኢንቨስተሮች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ በቅንጅት መሥራት የሚያስችል /Ethiopian Investment Deal Book/ አሳተመን ወደ ሥራ ገብተናል ብለዋል፡፡ በዚህም በኢትዮጵያና የአውሮፓ ህብረት ቢዝነስ ፎረም ከ100 በላይ ዓለም አቀፍ የአውሮፓ ኩባንያዎች የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጮች ለማየት መምጣታቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንትን የሚስቡ በርካታ ሪፎርሞች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ ሪፎርሙ የዓለም አቀፍ ኢንቨስተሮችን ቀልብ እየሳበ ነው ብለዋል፡፡ የንግድ ምክር ቤቱ ነባር አባላትን መከታተል ብቻ ሳይሆን አዳዲስ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ እንዲሰማሩ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወሳኝ የፖሊሲ እርምጃዎችን እና ግልጽ አሰራሮችን በመዘርጋት ለኢንቨስትመንት ምቹ ከባቢ መፍጠሯን ገልጸው፤መንግሥት ለግሉ ዘርፍ በሰጠው ትኩረት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ያለባቸው ጊዜ ነው ብለዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
በሲዳማ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ200 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ ገብተዋል
Apr 26, 2026 86
ሐዋሳ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ200 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሻግሬ ጀንበሬ አስታወቁ። የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነት ለማሳደግ ከቦታና ኃይል አቅርቦት ባለፈ የድጋፍና ክትትል ሥራ መከናወኑን ኃላፊው ለኢዜአ ተናግረዋል። ወደ ሥራ የገቡት አዳዲስና ነባር ኢንዱስትሪዎችም ከ20 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥረዋል ብለዋል። የወጪና ተኪ ምርቶች በማምረት ለሀገራዊ ዕድገቱ የበኩላቸውን ሚና እያበረከቱ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። የፀሐይ ቴክ ኢንጂነሪንግና የፈርኒቸር ሥራዎች ማኔጅንግ ዳይሬክተር ተመስገን አስፋው እንደገለጹት፤ መንግሥት ባደረገላቸው ድጋፍ በአጭር ጊዜ ወደ ሥራ ገብተው ውጤታማ ሆነዋል። ኤሊያና የወረቀት ማምረቻ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ ደረጀ ሞገስ በበኩላቸው፤ መንግሥት የብድር፣ የመስሪያ ማሽን እንዲሁም የኃይልና የቦታ አቅርቦት ድጋፍ እንዳደረገላቸው ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም ፋብሪካው ከ150 ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን አመላክተዋል።
የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት አቅም ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር በትብብር ላይ የተመሠረተ የኢኮኖሚ ዕድገትን እያፋጠነ ነው-ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)
Apr 26, 2026 89
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት አቅም ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር በትብብር ላይ የተመሠረተ የኢኮኖሚ ዕድገትን እያፋጠነ እንደሚገኝ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ። በዓባይ ወንዝ ላይ የተበሰረው ሕዳሴም የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት የተሳሳተ ትርክት መስበር ያስቻለ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱንም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን በመረቁበት ወቅት፤ የሀገራዊ ለውጡ የኢነርጂ ዘርፍ ሪፎርም የኢትዮጵያን የኃይል ሽግግር ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯል ብለዋል። በዚህም ከለውጡ በፊት የነበረው 4 ሺህ ሜጋ ዋት የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት አቅም ግዙፍ ፕሮጀክቶች በማሳካት አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት በማሳደግ እመርታዊ ውጤት መምጣቱን አስታውቀዋል። በኢነርጂ ዘርፍ የተሰራው ውጤታማ ሪፎርም የብሔራዊ የኃይል ቋት አቅርቦትና ሥርጭት አቅም በማጎልበት ህብረተሰቡን ከዋናውና አማራጭ የኃይል አቅርቦት ምንጮች ተጠቃሚ እያደረገ ነው። የኢትዮጵያ የኢነርጂ እመርታም ከራሷ አልፎ ለጎረቤቶቿ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርን በማፋጠን ለአህጉራዊ የኢኮኖሚ ውህደት መሳለጥ ገንቢ ሚና እየተወጣች ይገኛል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ የሪፎርም እመርታዊ ውጤት የኃይል አቅርቦት አቅምን መገንባት እያስቻለ ነው። ለአብነትም በውስብስብ የግንባታ ሂደት የነበረውን ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በማጠናቀቅ የኢትዮጵያን የኃይል አቅርቦት አቅም ከእጥፍ በላይ ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅም የኢትዮጵያን የኃይል ሽግግር በማፋጠን ለጎረቤት ሀገራትን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያሳልጥ ትሩፋት እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ በዝቅተኛ ዋጋ የምታቀርበው የኃይል አማራጭ ከቀጣናው ሀገራት ጋር በትብብር ለማደግ ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የጋራ ብልፅግናን የማፋጠን ፅኑ ፍላጎት አላት ያሉት ሚኒስትሩ፤ ነገር ግን ታሪካዊ ጠላቶች በሚሸርቡት ሴራ የተፈጥሮ ፀጋዎቿን ሳትጠቀም እንድትቆይ አድርገዋታል ብለዋል። በሀገራዊ ለውጡም ኢትዮጵያዊያን ሕዳሴን በዓባይ ላይ እውን በማድረግ የታሪካዊ ጠላቶችን የማይታለፍ የሚመስል ሴራ በድል መሻገር እንደቻሉ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የፓን አፍሪካኒዝም ግዙፍ ፕሮጀክት ስኬትም ለአፍሪካዊያን የመነሳት ዘመን ምሳሌና ቀጣናዊ ኃይል አቅርቦት ማማ እንድትሆን ማስቻሉን ተናግረዋል። በዓባይ ላይ ለስኬት የበቃው የሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን ከባሕር በር ለማራቅ የተሄደበትን የተሳሳተ ትርክት በመስበር በሁለቱ ውሃዎች ወግ አዲስ ምዕራፍ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን የውሃ ሃብት ጸጋዎች በሚገባ በማልማት ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
የእሁድ እይታዎች
Apr 26, 2026 209
የላቀ ስኬት ራሱን የመግለጥ ተፈጥሮ አለው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ውጤት የዓለምን ትኩረት ስቧል። በቅርቡ የአፍሪካ ኅብረት ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ሻምፒዮን አድርጎ መሾሙ፣ ቀደም ሲል የተቀበሏቸው የአለም የምግብና እርሻ ድርጅት (FAO) ሽልማት፣ የአግሪኮላ ሜዳሊያ፣ የላቀ የአፍሪካ መሪነት ሽልማት እና የኢጋድ (IGAD) የቱሪዝም ሻምፒዮንነት እውቅናዎች ላይ የተጨመረ ማረጋገጫ ነው። እነዚህ የክብር እና የአፈጻጸም እውቅናዎች የግል ስኬቶች ብቻ ሳይሆኑ፣ ኢትዮጵያ በቁልፍ ዘርፎች እያሳየች ያለችውን ከፍ እያለ የመጣ የመሪነት ሚና የሚያረጋግጡ ናቸው። የአፍሪካ ኅብረት ሹመት በዲጂታል ፈጠራ የታገዘውን ሰፊ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የሚያንጸባርቅ ነው። ኢትዮጵያን "ዘግይቶ ከመድረስ ዕዳ ወደ ቀድሞ መድረስ በረከት" ለማሸጋገር በተቀመጠው ርዕይ መሠረት፣ ሀገሪቱ በፈጠራ እና ቴክኖሎጂዎች ግንባር ቀደም ለመሆን ደፋር እርምጃዎችን ወስዳለች። የአፍሪካ የመጀመሪያውን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት የመሰረተችው ኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ የመጀመሪያውን፣ በዓለም ደግሞ ሁለተኛ የሆነውን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲም በመገንባት ላይ ትገኛለች። በተመሳሳይ በዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በበይነ መረብ የመንግሥት አገልግሎት (e-government) እና በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ እየተደረጉ ያሉ ኢንቨስትመንቶች ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኙ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ከ132 በላይ ተቋማት በፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ሥርዓት ስር ተሳስረዋል። በ31 የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች አማካኝነትም ከ476 ተቋማት የሚገኙ 2,396 አገልግሎቶች ለሕዝብ ተደራሽ ሆነዋል። ይህም ቢሮክራሲያዊ እንቅፋቶችን በእጅጉ ቀንሷል።ከ41 ሚሊዮን በላይ የፋይዳ መታወቂያ ተጠቃሚዎች እና 58 ሚልዮን የሞባይል ገንዘብ ደንበኞች መኖራቸው የጥሬ ገንዘብና በአካል በመገኘት የሚከናወኑ የአሠራር ችግሮችን እየቀረፉ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ራሷን ከመለወጥ ባለፈ፣ የ2030 የዲጂታል ግቦችን ለማሳካት ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ የአፍሪካን ዲጂታል ዘርፍ የወደፊት ዕጣ ፈንታ በመቅረጽ ላይ ትገኛለች። ርዕይን ፈጽሞ በመገኘት ጉልህ ዐሻራን እያሳረፈ የሚገኘው የአመራር ቁርጠኝነት ከቴክኖሎጂ ባሻገር፣ በአካባቢ ጥበቃ ረገድም ግልጽ ውጤት አሳይቷል። በ2011 የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ፣ ኢትዮጵያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማስተባበር የደን ጭፍጨፋን እና የአፈር መሸርሸርን መግታት ችላለች። በዚህም በስድስት ዓመታት ውስጥ የደን ሽፋኗን ወደ 23% አሳድጋለች። በፖሊሲ ተደግፎ የተጀመረው ይህ ንቅናቄ ወደ ሀገራዊ ባህል በመሸጋገሩ ለወጣቶችና ለሴቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ሥነ-ምህዳርን በማደስና የአካባቢ ጥበቃን ከሀገራዊ ጸጋ ጋር በማስተሳሰር ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ለዚህም እውቅና ይሆን ዘንድ፣ የተባበሩት መንግሥታት የምግብና እርሻ ድርጅት (FAO) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ለዘላቂ የደን ልማት የ2025 የስኬት ሽልማት አበርክቶላቸዋል። ከ2011 ጀምሮ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በመተከላቸው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ለሰፊ የአካባቢ ጥበቃ ሥራ የአኅጉሩ ተምሳሌት ሆናለች። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ተሟጋችነት ያላትን ሚና ከተሳታፊነት ወደ መሪነት ቀይሮታል። ሀገራችን አሁን ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ውይይቶችን የምታስተናግድና የምትመራ ሲሆን፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ከኢኮኖሚ ጥንካሬ፣ ከምግብ ዋስትና እና ከሀገራዊ አንድነት ጋር እንዴት እንደሚጣጣም በተግባር እያሳየች ነው። የዜጎች ተጠቃሚነትን በተመለከተ፤ የውኃ ተፋሰሶች መታደስ፣ የምግብ ሥርዓት መረጋጋት እና የአረንጓዴ የሥራ ዕድሎች መስፋፋት ተጨባጭ ጥቅሞች እየሰጡ ለመቀጠላቸው በርካታ አብነቶች አሉ። የኢትዮጵያ ለውጥ ቱሪዝምንና የከተማ ማደስ ሥራዎችንም ይጨምራል። በ2017 በኢጋድ የቱሪዝም ሻምፒዮን ተብለው የተመረጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የተፈጥሮ ቱሪዝምን፣ የከተማ ውበትንና የመሠረተ ልማት ዝርጋታን አፋጥነዋል። ቱሪዝም አሁን ላይ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ከተሞችን በማነቃቃትና ኢትዮጵያንና የአፍሪካ ቀንድን ተመራጭ የዓለም የቱሪስት መዳረሻ በማድረግ ረገድ የዕድገትና የቀጣናዊ ትስስር ሞተር ሆኗል። በግብርናው ዘርፍም የተመዘገቡት ውጤቶች ጉልህ ድርሻ ይዘዋል። በጥር 2016 ጠቅላይ ሚኒስትሩ የግብርናውን ዘርፍ በመለወጣቸው ከዓለም አቀፉ የእርሻ እና የምግብ ድርጅት ከፍተኛውን ክብር የአግሪኮላ ሜዳሊያ ተቀብለዋል። በ"ስንዴ ለምግብ ሉዓላዊነት" መርሃ ግብር አማካኝነት የእርሻ መሬት የሰፋ ሲሆን፣ ዓመታዊ የስንዴ ምርት በ2010 ከነበረበት 27 ሚሊዮን ኩንታል በ2017 ወደ 280 ሚሊዮን ኩንታል አድጓል። ይህ ለውጥ ከውጭ የሚገባ ምርትን ከመቀነሱም በላይ የገበሬውን ገቢ በመጨመር ኢትዮጵያ በስንዴ ራሷን እንድትችል አድርጓል። እነዚህ እውቅናዎች የኢትዮጵያን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ውጤታማነት የሚያረጋግጡ፣ ሀገሪቱን ለአኅጉራዊ የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና ለምግብ ሉዓላዊነት ዓርአያ ያደረጉ ናቸው። በዲጂታል ፈጠራ፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና በግብርና የታየው አንድ ግልጽ እውነታ፤ በጠንካራ አፈጻጸም የታገዘ ርዕይ መኖሩ ነው። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አመራር ታላቅ ዓላማ ከተግባር ጋር ሲዋሃድ እውቅና እና ሽልማት ተከትሎ እንደሚመጣ ያሳያል። እውቅናው በራሱ ግብ ሳይሆን፣ የተመዘገበው እውነተኛና ሊለካ የሚችል ለውጥ ማረጋገጫ ነው። እነዚህ ስኬቶች ከሽልማት በላይ፣ አንድን ሕዝብ ከፍ የሚያደርጉና የሀገሪቱን የወደፊት የዕድገት አቅጣጫ የሚቀርጹ ዘላቂ መሠረቶች ናቸው! #PMOEthiopia
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
መንግስት ለወጣት የዲጂታል ሥራ ፈጣሪዎች ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር ባለፈ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ ነው
Apr 25, 2026 347
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መንግስት ለወጣት የፊንቴክ ስታርትአፖች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር ባለፈ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢንተርፕሪነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት (EDI) እና ከተባበሩት መንግሥታት ካፒታል ልማት ፈንድ (UNCDF) ጋር በመተባበር፣ ላቅ ያለ የፈጠራ ሥራ ላሳዩ ስምንት የፊንቴክ (FinTech) ስታርትአፖች የገንዘብ ሽልማት መርሀ ግብር አካሂዷል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ መንግሥት ለወጣት የዲጂታል ሥራ ፈጣሪዎች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር ባለፈ ተገቢውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። መርሐ ግብሩ በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍን ለማዘመንና የወጣቶችን የፈጠራ አቅም ለማበረታታት ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል። የፊንቴክ መፍትሔዎች ለግብርና፣ ለቱሪዝም፣ ለኢንዱስትሪና ለጠቅላላው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ያላቸው ፋይዳ የላቀ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። ለዚህም በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ እንደ ቴሌ ብር እና ሲቢኢ ብር ያሉ ውጤቶች ለበርካታ ዜጎች የፋይናንስ ተደራሽነትን ማሳደጋቸውን በአብነት ጠቅሰዋል። የዘርፉን ተደራሽነት ለማስፋት ወጣቶች የሚፈጥሯቸው ዲጂታል መፍትሔዎች ለዲጂታል ሽግግር ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አስገንዝበዋል። ከ300 በላይ የፊንቴክ ስታርትአፖች መካከል 33ቱ ተለይተው ለፉክክር መቅረባቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በዛሬው ዕለት ስምንት ምርጥ ስራ ፈጣሪዎች አሸናፊ በመሆን ከአጋር ድርጅቶች የተገኘውን የ20 ሚሊዮን ብር ሽልማት አግኝተዋል ብለዋል። አሸናፊዎቹ የተሰጣቸውን የገንዘብ ድጋፍ የንግድ ሞዴሎቻቸውን በተጨባጭ የገበያ ሁኔታ ለመፈተሽና ለማሳደግ እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል። ከተሸላሚዎቹ መካከል የአበዳሪ መተግበሪያ ፈጣሪ ፌቨን ሽመልስ እና የኡጆ መተግበሪያ ፈጣሪ አቤኔዘር እንግዳ፣ መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት አድንቀዋል። ከተሸላሚዎቹ መካከል የ"አበዳሪ" መተግበሪያ ፈጣሪ ፌቨን ሽመልስ በበኩሏ፤ የብድር አቅርቦትና አሰባሰብን የሚያቀላጥፍ ቴክኖሎጂ በማበልጸግ ለዘርፉ መፍትሄ ማቅረቧን ገልጻለች። በተመሳሳይ የ"ኡጆ" መተግበሪያ ፈጣሪ አበኔዘር እንግዳ፣ ባህላዊውን የዕቁብ ሥርዓት በቴክኖሎጂ ለማዘመን ለጀመረው ሥራ መንግሥት የሰጠውን ትኩረትና ድጋፍ አድንቋል። ሽልማቱ ለጀመሩት የፈጠራ ሥራ መነሻ ካፒታል ከመሆኑ ባለፈ፤ ለሌሎች ወጣቶችም ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትና አላስፈላጊ ወጪን አስቀርቶልናል - ተገልጋዮች
Apr 25, 2026 107
ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልት እና ያልተገባ ወጪን እንዳስቀረላቸው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ከተማ ተገልጋዮች ገለፁ፡፡ በማዕከሉ አገልግሎት በማግኘት ላይ የነበሩት አቶ ዮናስ ሴራሞ ለኢዜአ እንደገለፁት ፤የገቢ ግብር ጉዳይ ላይ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ማዕከሉ እንደመጡና ባጠረ ጊዜም የሚፈልጉትን ፈጽመው ለመመለስ መቻላቸውን ነው የሚገልጹት። የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተገልጋይን ከአላስፈላጊ ከሆነ እንግልትና ወጪ እንደሚታደግ በተግባር ያረጋገጡ መሆኑንም ተናግረዋል። የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ለማውጣት ወደ ማዕከሉ የመጣው ወጣት ሞላልኝ ታምራት በወቅቱ አገልግሎቱን ማግኘቱን እና ማዕከሉ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ይታይ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር በመቅረፍ ለማሕበረሰቡ አስፈላጊ የሆነ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ነው የገለጸው። በማዕከሉ የተገልጋዩን ክብር የጠበቀ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኝቷ እንዳስደሰታት የምትገልፀው ደግሞ ወጣት በረከት ዱቲሶ ናት፡፡ በፋይዳ መታወቂያዋ ላይ ያጋጠማትን የስም ስህተት በአጭር ጊዜ ማስተካከል ችያለሁ ብላለች። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ከበደ ሻሜቦ ማዕከሉ በስምንት ተቋማት 27 አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ እስካሁን ድረስ ከ 20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠት መቻሉንም አስረድተዋል፡፡ በከተሞች በመሬት ዘርፍ የሚሰጡና ለብልሹ አሰራር ተጋላጭ የሆኑ አዳዲስ 48 አገልግሎቶች ተለይተዉ በማዕከሉ ውስጥ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻልም ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል፡፡
ተማሪዎች ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን እንዲያፈልቁ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል
Apr 25, 2026 125
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ ተማሪዎች ችግር ፈቺና ተወዳዳሪ የፈጠራ ስራዎችን እንዲያፈልቁ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን የከተማው ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ገለጹ። ቢሮው “በሳይንስና ፈጠራ የተካነ ትውልድ ለተምሳሌታዊ ሀገር” በሚል መሪ ሐሳብ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየው 11ኛው የሳይንስና የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ተጠናቋል። በአውደ ርዕዩም በተማሪዎችና መምህራን የቀረቡ የፈጠራ ሀሳቦች ተወዳድረው የላቀ ውጤት ላመጡ ተሳታፊዎች የሽልማት አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ተከናውኗል። የቢሮው ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ተማሪዎች ከቀለም ትምህርት ጎን ለጎን የፈጠራ ክህሎታቸውን አውጥተው እንዲጠቀሙ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በየዓመቱ የሚዘጋጀው ይህ የሳይንስና የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይም ተማሪዎችና መምህራን ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡና የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልፀዋል። ውድድሩ ተማሪዎችን በምርምርና በስልጠና በማገዝ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለመቅረፅ ያለመ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፤ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን በተግባር እንዲከውኑና ወደ ሳይንሳዊ ግኝት እንዲቀይሩ ትልቅ አቅም መፈጠሩን አስረድተዋል። በዘንድሮው አውደ ርዕይ ላይ ወደ 3 ሺህ 7 መቶ የሚጠጉ የፈጠራ ስራዎች ለውድድር መቅረባቸውን ጠቅሰው ከእነዚህም ውስጥ ከፍተኛ ውጤት ላመጡ አሸናፊዎች የእውቅና ሽልማት ተበርክቷል ብለዋል። መድረኩ ከውድድር ባለፈ ለብዙዎች የተሻለ ነገን በተስፋ ለመጠበቅ መሠረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመው፣ ለዚህም ስኬት ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ገልፀዋል። ከአውደ ርዕዩ ተሳታፊዎች መካከል የኢትዮ-ጃፓን 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሃብታሙ ደምስ ፤ለእርሻ አገልግሎት የሚውልና በፀሐይ ሃይል የሚሰራ ትራክተር በመስራት በውድድሩ የ1ኛ ደረጃ አሸናፊ ሆኗል። ተማሪ ሃብታሙ ፤ አርሶ አደሩ ከባህላዊ የእርሻ ዘዴ ተላቆ በቴክኖሎጂ ታግዞ እንዲያመርት ለማስቻል መሣሪያውን እንደሰራ ገልጿል። በተመሳሳይ የቡርቃ ዋዮ ትምህርት ቤት ተማሪ ፌኔት በንቲ፤ በስዕልና ቅርፃቅርፅ የፈጠራ ስራ ተወዳድራ የ2ኛ ደረጃ አሸናፊ መሆን ችላለች። ተሳታፊ ተማሪዎቹ እንደገለጹት፤ መሰል አውደ ርዕዮች ያላቸውን እምቅ አቅም አውጥተው እንዲጠቀሙና ከሌሎች ተማሪዎች ልምድ እንዲቀስሙ ትልቅ እገዛ እያደረገላቸው ይገኛል።
መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ፈጣን እና ጊዜ ቆጣቢ ነው- ተገልጋዮች
Apr 24, 2026 100
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ወደ እኛ ከመቅረቡም ባለፈ ፈጣን እና ጊዜ ቆጣቢ ሆኖ አግኝተነዋል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ የታመነበትን መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በይፋ መርቀው ሥራ ማስጀመራቸው ይታወቃል። በምረቃው ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፤ ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም ዜጎች ጊዜ ቆጣቢ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል በቁርጠኝነት እየተሠራ ይገኛል። የመሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት አጭር ጊዜ ቢሆንም፤ በአገልግሎቱ የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የሥራ ሞዴሉን ውጤታማነት በተግባር ማረጋገጡንም ጠቁመዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጀርመን አደባባይ አካባቢ ለህዝቡ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በዚሁ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች አገልግሎቱ ፈጣን እና ጊዜ ቆጣቢ መሆኑን ተናግረዋል። አቶ ኢብራሂም መሐመድ የመኪና ቦሎ ለማደስ ወደ ቦታው መሄዳቸውን ጠቁመው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ጨርሰው መመለሳቸውን ተናግረዋል። አቶ ብስራት ኮሬ እና አቶ ዘላለም አስረስም ለመንጃ ፈቃድና ለቦሎ ዕድሳት ወደ ተንቀሳቃሽ አውቶቡሱ በማቅናት፣ በአይነቱ ልዩና ቀልጣፋ መስተንግዶ ማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል። ያለምንም ስጋት ጊዜያቸውንም ቆጥበው በአገልግሎቱ ተጠቃሚ በመሆናቸው መደሰታቸውን ይናገራሉ። በተንቀሳቃሽ አገልግሎቱ ውስጥ የሚሰሩት የገቢዎች ባለሙያ ጫልቱ ታደሰ፣ ይህ አሰራር የተለመደውን በአንድ ቦታ ተወስኖ የመስራት አካሄድ በመቀየር ለተገልጋዩ ብቻ ሳይሆን ለአገልጋዩም ከፍተኛ የስራ ተነሳሽነትን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። የንግድ ምዝገባ እና ፍቃድ ባለሙያ ብርሃኑ ፈንታው በበኩላቸው፣ ወደ ተገልጋዮች ቀርበው በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የመጀመሪያዎቹ ባለሙያዎች በመሆናቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ካባ መብራቱ፤ የመሶብ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ቀደም ሲል በሕዝብ ዘንድ ይነሳ የነበረውን ቅሬታ ለመፍታት መንግሥት የወሰደውን ቁርጠኛ አቋም የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። አዲሱ እሳቤ አገልግሎትን ከቢሮ በማውጣት ወደ ሕዝብ ይዞ የመጣ ድንቅ አሠራር መሆኑን አረጋግጠዋል።
ስፖርት
በለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀቀ
Apr 26, 2026 63
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 18/2018(ኢዜአ)፦በተጠባቂው የወንዶች የለንደን ማራቶን ውድድር በለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል። በ46ኛው የለንደን ማራቶን የወንዶች ምድብ ውድድር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ውድድሩን 1:59.41 በመግባት ሁለተኛ ወጥቷል። ኬንያዊው አትሌት ሴባስቲያን ሳው ውድድሩን በበላይነት ሲያጠናቅቅ ዩጋንዳዊው ጃኮፕ ኪፕሊሞ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በሴቶች የለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ትዕግስት አሰፋ አሸነፈች
Apr 26, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 18/2018(ኢዜአ)፦ በተጠባቂው የሴቶች ለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ትዕግስት አሰፋ አሸንፋለች። በ46ኛውን የለንደን ማራቶን የሴቶች ምድብ ውድድር የፓሪስ ኦሎምፒክ የብር ሜዳልያ ባለቤቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ በበላይነት አሸንፋለች። አትሌት ትዕግስት አሰፋ ውድድሩን 2:15፡41 በሆነ ሠዓት በመግባት ነው ውድድሩን በበላይነት ጣጠናቀቀችው። በዚሁ ውድድር ኬንያውያኑ አትሌቶች ሐለን ኦቢሪ ሁለተኛ እንዲሁም ጆይሲሊን ጄፕኮስጊ ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ታላቁ ሩጫ ኢትዮጵያን በማስተዋወቅ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው
Apr 26, 2026 62
ጅማ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ) የቱሪዝም ሚኒስቴር ታላቁ ሩጫ ኢትዮጵያን በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገለጸ። ዛሬ በጅማ ከተማ "ፖሊዮን በጋራ እናጥፋ" በሚል መሪ ሐሳብ የ15 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ተካሂዷል። በውድድሩ ላይ ከ10 ሀገራት የተውጣጡ እና ቁጥራቸው ከ4 ሺህ በላይ ተወዳዳሪዎች ተሳትፈዋል። የቱሪዝም ሚኒስቴር ተወካይ ተሾመ ተክሉ በዚሁ ወቅት፤ ታላቁ ሩጫ ኢትዮጵያን በማስተዋወቅ ትልቅ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። በየዓመቱ የተሳታፊዎች ቁጥር ከፍ እያለ መምጣቱን ጠቅሰው፤ በክልል ከተሞች መካሄዱ ከተሞቻችንን ለማስተዋወቀ ያግዛል ብለዋል። የፖሊዮ በሽታ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት የሚያስከትል አደገኛ በሽታ መሆኑን የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ተወካይ ደግሰው ደርሶ በበኩላቸው፤ የሚታየውን የግንዛቤ እጥረት ለመቅረፍና የክትባት ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በውድድሩ የጤና ተሳታፊዎች ፖሊዮን የማጥፋት መልዕክት በሩጫው ላይ አስተላልፈዋል። የኢትዮቴሌኮም ደቡብ ምዕራብ ሪጅናል ዳይሬክተር ክፍሌ ካሳ ስፖርት ትውልድን በመገንባት ሂደት ውስጥ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፤ ተቋማቸው እንደዚህ ያሉ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮግራሞችን በመደገፍ በጋራ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ውድድሩን በወንዶች ጃፈር ጀማል እንዲሁም በሴቶች የግሌ እሸቱ ያሸነፉ ሲሆን፤ የሜዳሊያና ሌሎች ሽልማቶችም ተበርክቶላቸዋል።
የኢትዮጵያ ከተሞች ዕድገት የሚደነቅ ነው - የታላቁ ሩጫ በጅማ ተሳታፊዎች
Apr 26, 2026 85
ጅማ፤ ሚያዝያ 18/2018 (ኢዜአ) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዕየታየ ያለው የኢትዮጵያ ከተሞች ዕድገት የሚደነቅ መሆኑን የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ታላቁ ሩጫ በጅማ 2018 ተሳታፊዎች ተናገሩ። የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ታላቁ ሩጫ በጅማ 2018 የ15 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑት ሳምሶን ዘለቀ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በጅማ ከተማ ለውጥ እጅግ መደነቃቸውን ተናግረዋል። በፍጥነት እየተገነቡ ያሉ መሠረተ-ልማቶች የከተማዋን ዕድገት እያፋጠኑ መሆኑንም ጠቅሰዋል። አንዳንድ የሀገራችንን ከተሞች ተመልክቻለሁ ያሉት አቶ ሳምሶን፤ ከዓመታት በፊት ከነበሩት ተለውጠው አሁን ላይ ፅዱና ማራኪ መሆናቸውን በመጥቀስ በዚህም መደነቃቸውን ገልጸዋል። ሌላኛው የአዲስ አበባ ነዋሪ እና ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ጅማን የተመለከቱት ዮሐንስ አየልኝ፤ የከተማዋ ለውጥ እና የኮሪደር ልማት አስገራሚ መሆኑን ይናገራሉ። ከተሞችን በማስዋብ እና በማስተዋወቅ የቱሪዝም ዘርፉን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸው፤ በዚህ ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አመላክተዋል። በኢትዮጵያውያን የእንግዳ አቀባበልና በተመለከቱት የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት መደነቃቸውን የተናገሩት ደግሞ ፊንላንዳዊቷ ኪራ ፓካሪ ናቸው። ጅማ ውብ ሆና መገኘቷን አድንቀው፤ ሌሎች ከተሞችም በዚሁ ልክ እየለሙና እየተለወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። ጣሊያናዊው አልቤርቶ በሰጡት አስተያየት ደግሞ ከዓመት በፊት ወደ ጅማ ከተማ መጥተው እንደነበር በማስታወስ፤ እየተገነቡ የነበሩ የተለያዩ መሠረተ-ልማቶች አሁን ተጠናቀው የከተማዋን ገፅታ መቀየራቸው እንዳስደነቃቸው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚያደርጉት እንቅስቃሴ እንደሚያስደስታቸውም አመላክቷል።
አካባቢ ጥበቃ
ለአረንጓዴ አሻራ ልማት ስኬት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚና ላቀ ነው
Apr 24, 2026 114
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ለምግብ ዋስትና መሰረት ለሆነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስኬት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የላቀ ሚናቸውን ማስቀጠል እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ፡፡ የክልሉ ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ከክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ጋር በመተባበር በአረንጓዴ አሻራ ልማት ዙሪያ ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በሆሳዕና ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር እንደገለጹት፤ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ ትግበራ ከደን ልማቱ ባለፈ የስነ ምግብ ዋስትና መሰረት እየሆነ መጥቷል። በልማቱ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ያላቸውንና ለምግብ የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎችን በብዛትና በስፋት የማልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ለተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ለምግብ ዋስትና መሰረት ለሆነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስኬት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አንስተዋል። የስልጠናው ዓላማም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በእውቀትና መረጃ ላይ የተመሰረተ መረጃ ለህዝብ ተደራሽ ማድረግ እንዲችሉ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ዘሪሁን እሸቱ፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን በሚገባ ተገንዝበው የተሟላ መረጃ ለህዝብ ተደራሽ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። ለዚህም መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ወሳኝ እንደሆኑ አንስተው በቀጣይም በሙያቸው የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ በማስቀጠል ልማቱን እንዲያጠናክሩ አስገንዝበዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት፤ የኮሙኒኬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ ይኖራቸዋል
Apr 24, 2026 117
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረውን የአየር ሁኔታ ትንበያ አስመልክቶ ለኢዜአ መግለጫ ልኳል፡፡ በዚህም በሚቀጥሉት አስር ቀናት በርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚያገኙ አመላክቷል፡፡ በመግለጫው በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል፣ የስምጥ ሸለቆና አጎራባች አካባቢዎች፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እንዲሁም ሰሜን ምዕራብ እና ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚኖራቸው አስታውቋል፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች የሚኖረው ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ለቋሚ ተክሎች ዕድገት፣ ለግጦሽ ሳርና ለውሃ አቅርቦት መሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጿል። በሌላ በኩል ከዝናቡ ጋር ተያይዞ የመሬት መንሸራተት፣ የአፈር መሸርሸር እና ድንገተኛ ጎርፍ አደጋዎች ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ብሏል፡፡ በተጨማሪም በተደፋታማ ማሳዎች ላይ ውሃ መተኛት፣ የሰብል በሽታና ተባይ መከሰት እንዲሁም የአረም መስፋፋት ሊከሰት እንደሚችል ጠቅሷል፡፡ በዚህም በከተሞች በቆሻሻ የተደፈኑ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦዎችን ማጽዳትና የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎችን መሥራት ይገባል ብሏል በመግለጫው፡፡ የአፈርና ውሃ እቀባ ስራዎች እንዲሁም የእርከን ስራዎችን ማጠናከር፣ የሰብል በሽታና አረምን አስቀድሞ መከላከል እንዲሁም የእንስሳት መኖ መሰብሰብ እንደሚገባም አመላክቷል፡፡ በተጨማሪም ዝቅተኛ እርጥበት በሚገኝባቸው አካባቢዎች የዝናብ ውሃን በማሰባሰብና ደጋፊ መስኖን በመጠቀም የትነት መጠን የሚያስከትለውን ጉድለት መሙላት እንደሚገባ አስታውቋል፡፡ በአባይ፣ ባሮ አኮቦ፣ የላይኛው ኦሞ ጊቤ፣ ገናሌ ዳዋ እና ስምጥ ሸለቆ ተፋሰሶች ላይ ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ የገፀ-ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖርም በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ይህም ለኃይል ማመንጫ፣ ለመስኖና ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሻሻል ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁሞ፤ ህብረተሰቡ የጎርፍ አደጋን ለመከላከልና የሚገኘውን እርጥበት በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባውም አሳስቧል፡፡
በብሔረሰብ አሥተዳደሩ ሥነ-ምኅዳርን መሠረት ያደረጉ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው
Apr 24, 2026 104
ሰቆጣ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በመጪው ክረምት ሥነ-ምኅዳርን መሠረት ያደረጉ ችግኞችን ለመትከል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የዋግኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የደን ባለሙያ ታደሠ መሳይ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ አሥተዳደሩ ዝናብ አጠር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የተፈጥሮ ሃብት ሥራና የደን ልማት ተግባራት በከፍተኛ ትጋት እየተሠራበት ነው። በዚህም እስካሁን 3 ነጥብ 7 ሚሊየን ችግኞችን ለተከላ ዝግጁ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው፤ ችግኞቹ ምኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውና ሀገር በቀል ናቸው ብለዋል። በበጋው ወራት የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ የተሠራበትን ጨምሮ ከ2 ሺህ 130 ሔክታር በላይ መሬት በመለየት የችግኝ መትከያ ጉድጓድ የማስቆፈር ሥራ እየተሠራ መሆኑንም አስረድተዋል። ባለፉት ዓመታት ሥነ-ምኅዳሩንና የአየር ንብረቱን መሠረት ያደረጉ ችግኞችን በመትከል አካባቢውን ወደ ምርታማነት የመለወጥ ሥራ ውጤት በማሳየቱ፤ ሕብረተሰቡ ለተፈጥሮ ሃብት ሥራ ከፍተኛ ፍላጎት ማሳየቱን ጠቁመዋል።
በምሥራቅ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ ነው
Apr 23, 2026 115
ነቀምቴ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦በምሥራቅ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። በጽሕፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ በለጠ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ ነው። በዘንድሮው መርሐ ግብር ለሁሉም የችግኝ ዓይነቶች ትኩረት ቢሰጥም፣ ይበልጥ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ዝርያዎች ላይ ትኩረት ተደርጓል ነው ያሉት። እየፈሉ ከሚገኙት ችግኞች መካከል አትክልትና ፍራፍሬ፣ የደንና ጥምር ደን ዝርያዎች፣ ቀርከሃ፣ የእንስሳት መኖ የሚገኙበት መሆኑን ነው የተናገሩት። የእጽዋት ስብጥሩ ከአካባቢው አየር ንብረት ጋር የሚስማማና በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤት የሚሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ካለፉት ዓመታት ተሞክሮ በመነሳት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የጉድጓድ ዝግጅት መጀመሩን የጠቆሙት አቶ ደሳለኝ፤ የአየር ንብረት ጥናት፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ እንዲሁም የሕብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያሳድጉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። ለዘንድሮው ተከላ የሚውል 107 ሺህ ሄክታር መሬት የተዘጋጀ ሲሆን፣ በዞኑ በሚገኙ 2 ሺህ 194 የመንግሥትና የግል የችግኝ ጣቢያዎችም የችግኝ እንክብካቤ ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው ችግኝ መትከል ከመደበኛ መርሐ ግብር ባለፈ የሥራ ባሕላቸው እየሆነ መምጣቱን ይናገራሉ። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ወይዘሮ አዲስዓለም በለጠ ባለፉት ዓመታት በተተከሉ ችግኞች በአካባቢው የተፈጥሮ ሀብት ለውጥ መታየቱን ገልጸዋል። አቶ ተሰማ መኮንንም በተመሳሳይ ቀደም ሲል ለደን የነበረው ዝቅተኛ አመለካከት ተቀይሮ፣ ዛሬ ሕብረተሰቡ የተራቆቱ ቦታዎችን መልሶ በማልማትና በመንከባከብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለዘንድሮው ተከላም አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 493
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 397
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 685
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት። ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው
Mar 22, 2026 378
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሐተታዎች
ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር
Apr 23, 2026 235
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት በቢሾፍቱ ከተማ በይፋ መጀመሯን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል። ጋዜጠኛ ዳንኤል ኦሊቫሬስ ጋሌጎ በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ እንደገለጸው፣ ይህ ሜጋ ፕሮጀክት አፍሪካውያን ተጓዦች ከአህጉሩ ውጭ ባሉ እንደ ዱባይ፣ ፓሪስና ለንደን ባሉ ማዕከላት በኩል የሚያደርጉትን አድካሚ ጉዞ በማስቀረት፣ አዲስ አበባን የአህጉሪቱ ቀዳሚ የመገናኛ ማዕከል ለማድረግ ያለመ ነው። ከአዲስ አበባ ከተማ በስተደቡብ ምስራቅ 48 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ይህ ግዙፍ ግንባታ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ተብሎ መጠቀሱን ጋዜጠኛው በዚሁ ጽሁፉ አመልክቷል። ስራው በይፋ የተጀመረው ባለፈው ጥር ወር ሲሆን፣ አውሮፕላን ማረፊያው በ2023 ዓ.ም (2030 እ.ኤ.አ) የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር፣ በዓመት 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም እንደሚኖረው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ተመልክቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ፣ ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል። ይህም አውሮፕላን ማረፊያውን በዓለም ላይ በርካታ ተጓዦችን ከሚያስተናግደው የአትላንታው ሀርትስፊልድ-ጃክሰን አውሮፕላን ማረፊያ ካለው አቅም በላይ እንደሚያደርገው ዳንኤል ኦሊቫሬስ ጋሌጎ ባሰፈረው ጽሁፍ አብራርቷል። አውሮፕላን ማረፊያው ከመንገደኞች አገልግሎት ባለፈ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠናን (AfCFTA) በላቀ ሁኔታ ለመደገፍ ታቅዶ የተገነባ መሆኑን ጋዜጠኛው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ በዝርዝር አስቀምጧል። በዓመት 3 ነጥብ 73 ሚሊዮን ቶን ጭነት የማስተናገድ አቅም ያለው ይህ መሠረተ ልማት፣ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የአፍሪካን የጭነት በረራ ፍላጎት በሚገባ ምላሽ መስጠት የሚችል መሆኑን ተጠቁሟል። የአውሮፕላን ማረፊያው የተርሚናል ዲዛይን በዓለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ በሆነው ዛሃ ሃዲድ አርክቴክትስ የቀረበ መሆኑን የጠቀሰው ጋዜጠኛው፣ዲዛይኑ የኢትዮጵያን ታላቁ ስምጥ ሸለቆና የተለያየ መልክዓ ምድራዊ ውበትን የሚያንፀባርቅ መሆኑን በጽሁፉ አካቷል። ተጓዦች በአውሮፕላን ማረፊያው ውስጥ ሲዘዋወሩ የኢትዮጵያን ባህልና ተፈጥሮ እንዲመለከቱ በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን፣ለዘላቂነት ቅድሚያ በመስጠት የፀሐይ ብርሃን ኃይልንና የዝናብ ውሃ አሰባሰብ ስርዓትን እንዲጠቀም ተደርጎ ተቀርጿል። በአጠቃላይ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጠናቀቅ፣ኢትዮጵያ በአፍሪካ አቪዬሽን ያላትን መሪነት ከማረጋገጡ ባለፈ የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ትስስር ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ጋዜጠኛው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ደምድሟል። ይህ ፕሮጀክት ከሌሎች የአፍሪካ አየር መንገዶች ጋር በመተባበር የነጠላ የአፍሪካ አየር ትራንስፖርት ገበያን (SAATM) ወደ ተግባር ለመቀየር የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እንደሚያግዝም ተመልክቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 19, 2026 333
የምግብ ሉዓላዊነት - ከተረጂነት መላቀቂያው መንገድ በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ ከተረጂነትና ጠባቂነት መፋቻ መንገዶች መካከል የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አንዱ ብልኀት አድርጋ እየታተረች ነው። ይህን ተከትሎም የዜጎችን የምግብ ፍላጎት በራስ የምርት ዐቅም የመሸፈን ሥራ በመከወን ከጠባቂነት ለመላቀቅ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ስኬታማ ናቸው። ለዚህም ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ከልመና ወጥታ ወደ ውጭ ገበያ መላክ መጀመሯ አሥረጅ ነው። በመሆኑም ከውጭ የኢኮኖሚ ጥገኝነት በመላቀቅ የዜጎችን የምግብ ሉዓላዊነት ለማስከበር በስንዴ ልማት የተመዘገበውን ስኬት በሌሎች የግብርና ዘርፎች ለመድገም ርብርብ እየተደረገ ነው። በዚህም መሠረት በሩዝ፣ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ሻይ ቅጠል እና ሌሎች የተለያዩ ሰብሎች ላይ እየተከናወነ ያለው ሥራ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው። የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የግብርና ድርጅት (ፋኦ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምግብ ዋስትናና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ የአመራር ቁርጠኝነት የአግሪኮላ ሜዳሊያ በ2016 ዓ.ም ማበርከቱ ለምግብ ሉዓላዊነት ጥረት የተሰጠ ዕውቅና ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ረሃብን ከማስቀረት ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ብሔራዊ ብልጽግናን ዕውን ለማድረግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሃብቶች፣ተስማሚ የዓየር ንብረት፣ ለሥራ ትጉ የሆነ ወጣት እንዳላት እና እነዚህን ሃብቶች ታሳቢ በማድረግ የታሪክ ዐውራ የሆነችውን ሀገር ልማት ወደፊት ለማራመድ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል። በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ እንደከፈልን ሁሉ፤ ከምግብ ጥገኝነት ለመላቀቅ በትጋት መሥራት ይገባል ሲሉ ማስገንዘባቸው ይታወሳል። የምግብ ሉዓላዊነት፣የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት፣ የበጀት ሉዓላዊነት ታላቁን የሀገር ሉዓላዊነት በጽናት የሚያቆሙ መሆናቸውንም አብራርተዋል። እነዚህን የሉዓላዊነት ዘርፎች ለማስከበርም ብሔራዊ ዐርበኝነት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። ሀገራዊ ትልሙ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት የሚያሸጋግር መልካም ጅማሮ ነው።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 19, 2026 167
ክልሎች፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የንፋስ ሃይል በቀጥታ የምናመራው በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ አካባቢ ነው። በኢተያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው የመረቁትን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን እንመለከታለን። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 100 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ሲሆን ኢትዮጵያ በታዳሽ ሃይል ልማት ወደ ፊት እየተራመደች መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ሥራ ነው። ኢትዮጵያ ዘንድሮ ከጉባ እስከ አሰላ፣ ገናሌ እና አይሻ በሃይል ልማት ዘርፍ ትልቅ ትርጉም ያላቸውን ፕሮጀክቶች አስመርቃለች። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ደግሞ በዚህ ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀምሯል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በምርቃቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ከለውጡ በፊት የነበረው 4 ሺህ ሜጋ ዋት የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅም አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት በመድረስ ከእጥፍ በላይ እድገት የተመዘገበበትን ትልቅ ስኬት አንስተዋል። የስንዴና ገብስ ሰብሎችን በከፍተኛ መጠን የሚያመርተው አርሲና አካባቢው አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ሃይል የሚመረትበት አካባቢ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ እናስቀጥላለን ሲሉ አረጋግጠዋል። ቢሾፍቱ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማም በዚህ ሳምንት በቢሾፍቱ ሀርሰዴ አዳራሽ መካሄዱ ይታወቃል። በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ስኬታማ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በተለይም የክልሉን ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተሻለ መልኩ ያሳደጉ የከተማ እና የገጠር የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ነው ያስረዱት። ከዚህ ባለፈ የክልሉን የልማት ሥራዎች ለማቀላጠፍ የሚያግዙ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የአገልግሎት አሰጣጥ አሰራሮች መተግበራቸውንም ተናግረዋል። የቢሾፍቱ መድረክ በድምሩ የግብርና፣ የገጠርና የከተሞች ልማት፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ክንውን በዝርዝር የታየበት ውጤታማ መድረክ እንደነበረም ተመላክቷል። የአሎማ ክላስተር ሌላ የሳምንቱ ዓበይት ጉዳይ ወደ አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ይወስደናል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በይፋ አገልግሎት መስጠት የጀመረው በዚህ ሳምንት ነው። በመስኖ የለማ የስንዴ ክላስተር የተጎበኘበትና በተሁለደሬ ወረዳ በክላስተር ለሚከናወነው የተቀናጀ የፍራፍሬ ልማት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ የተጀመረበት እንዲሁም የክልሉ የ10 ዓመት የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ ይፋ የተደረገበትን ሁነት እናገኛለን። በእነዚህ ሁነቶች ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የመደመር መንግሥት በሁሉም ዘርፎች ለሀገር እድገትና ማንሰራራት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም በግብርና፣ በመስኖ ልማት፣ በቱሪዝምና ሌሎች መስኮች በተግባር የተመለከትናቸው የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ማሳያዎች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። የአሎማ ክላስተር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የሓይቅ ዳር አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የማቻል ጥረት በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን የሚያሳዩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሀገርን የማሻገር ሥራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የታሪክ መሰነጃ የሳምንቱ በረራችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ የሰው ልጅ መገኛ፣ የኤርታሌ ትኩሳት የሚገነፍልባትና የአዋሽ ወንዝ የተንጣለለባት አፋር ክልል ገብተናል። በአፋር ቆይታችን ትኩረታችንን ሰመራ በማድረግ በስፍራው ሊገነባ የታሰበውን የሉሲ ሙዚየም እንመለከታለን። ሙዚየሙን ለመገንባት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እና የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ የፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት አድርገዋል። ለሉሲ አፋር ቤቷ ነው፤ ሀዳር የተባለው ስፍራ ደግሞ መገኛዋ ነው። በመሆኑም በዚህ ከሰው ልጅ መገኛ ጋር የተቆራኘን ስፍራ ሙዚየም ገንብቶ፣ የቱሪስት መስህብ አልምቶና አካባቢውን በስፋት አስተዋውቆ የገቢ ምንጭ ማድረግ ሲቻል ለምን ተዘንግቶ ቆየ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ይሆናል። የጊዜ ጉዳይ ሆኖ አሁን አፋር ሰመራ ላይ በሉሲ የተሰየመ የሀገር ታሪክና ቅርስ ማጣቀሻ፤ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ማሳያ የሆነ ሙዚየም ለመገንባት ዝግጅት መደረጉ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር)፤ የሚገነባው ሙዚየም የሀገር ታሪክና ቅርስ የሚሰነድበት፣ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ተጠብቀው የሚዘልቁበት፣ የሰው ልጅ አመጣጥና ዝግመተ ለውጥ የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ የሚካሄድበት ይሆናል ብለዋል። እሳቸው እንዳሉት የሙዚየሙ ግንባታ በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገለግሎት የሚበቃ ይሆናል። የአፋር ክልል በመስኖ ቢያለሙበት፣ የጥጥ እና የቴምር ልማት ቢካሄድበት ተዝቆ የማያልቅ እምቅ አቅም ያለው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በለውጡ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን እምቅ የቱሪዝም ሃብቱንም በማልማትና በመጠበቅ የሃገር ሃብት የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የሉሲ ሙዚየም ግንባታ ሁነኛ ማሳያ ነው። የሳምንቱ ቅኝታችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ በቀጥታ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ አሶሳ ተገኝተናል። አሶሳ በሳምንቱ በሃይማኖት አባቶች ጸሎትና ዱአ ተባርካ ስለ ሰላምና አብሮነት የሚመከርባት ከተማ ሆና እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። የተለያዩ የኃይማኖት አባቶች፣ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት 7ኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ "ሰላምን ይበልጥ ለማስፋት እና ለማስረጽ የሃይማኖቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ አባቶች ስለ ሰላም እና አብሮነት እንትጋ ለትውልድ ግንባታም መስራት ግድ ይለናል በማለት አፅንኦት በመስጠት መክረዋል። የኢትዮጵያ ሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ኃይማኖቶች ለሰላም እና ለህዝቦች አብሮነት ያላቸውን አስተምህሮ በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ እና ሀገራዊ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆን አለባቸው ብለዋል። በኢትዮጵያ ሰላምን ለማጽናት እና የወንድማማችነት ድልድይን ለመገንባት እንስራ በማለትም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ስንጓዝ የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ-AGRA) ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች የኤልቶ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ዩኒየን የሥራ እንቅስቃሴን መጎብኘታቸውን እናገኛለን። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጥምረቱ የቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ አርሶ አደሮች ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ጥሩ ተስፋ የተሰነቀበት መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። የግብርና ልማትን የማዘመን፣ ምርታማነትን የማሳደግና የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር መሆኑንም አፅንኦት ሰጥተዋል። የጥምረቱ ፕሬዚዳንት አሊስ ሩህዌዛ፤ በአፍሪካ የግብርና ስርዓት ሽግግርን ለማጠናከር በተለይም አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። በአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ሂደት ውስጥ ደግሞ የኢትዮጵያ ለውጥ አስደናቂ ስለመሆኑ አንስተዋል። ሌሎች በዚህ ሳምንት በሁሉም ክልሎች ባደረግነው ምልክታ በተለይም የምርጫ ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳ ሆኖ ዜጎች የምርጫ ካርዳቸውን እየወሰዱ ሲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎችም የምረጡኝ ቅስቃሳ ማድርጋቸውን ቀጥለዋል። የግብርና ልማት ስራዎች፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እና ሌሎችም የልማት ሥራዎች በተጠናከረ መልኩ የቀጠሉበት ሳምንት ነበር ማለት ይቻላል።
የጤና ነገር …
Apr 17, 2026 370
በዮሐንስ ደርበው ማዲያት ታክሞ ይድናል? እነማንንስ ያጠቃል? የሥነ-ውበት ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ሱመያ ኑርሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለማዲያት መንስዔ፣ ምልክቶች እና ሕክምና ሙያዊ ሐሳባቸውን አጋርተዋል። እንደ ባለሙያ ቢደረግ ያሉትንም መክረዋል። • ማዲያት እነማንን ያጠቃል? ማዲያት ማንኛውንም ሰው እንደሚያጠቃ ያነሱት ዶ/ር ሱመያ፤ በብዛት ግን በሴቶች ላይ እንደሚከሰት ያስረዳሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ እርግዝና ላይ ያሉ እንዲሁም የወሊድ መከላከያ የሚወስዱ ሴቶች እና ሆርሞናል ቴራፒ ላይ ያሉ ሰዎች በስፋት ለማዲያት ተጋላጭ ናቸው። በተጨማሪም በብዛት ምግብ ማብሰል (ኪችን) ላይ የሚሠሩ ሰዎች ለማዲያት እንደሚጋለጡ ጠቁመዋል። ባብዛኛው ማዲያት የሚያጠቃው በዕድሜ ከ25 ወይም ከ30ዎቹ በላይ የሆኑትን መሆኑንም አንስተዋል። • መንስዔ እንደ ዶክተር ሱመያ ገለጻ፤ ለማዲያት ከሚያጋልጡ መንስዔዎች መካከል ዋነኛው የፀሐይ ጨረር ነው። በተጨማሪም ሆርሞናል ፋክተር (የወሊድ መከላከያ መጠቀም፣ እርግዝና ላይ መሆን፣ ሆርሞናል ቴራፒ መውሰድ) ለማዲያት አጋላጭ መንስዔ ሆነው ይጠቀሳሉ ይላሉ። ጭንቀት እንዲሁም ቆዳን የሚያስቆጡ ነገሮች ለማዲያት አጋላጭ መሆናቸውንም ነው ያብራሩት። • ምልክቶች ማዲያት ቀላ፣ ጠቆር ወይም ደብዘዝ ያለ ቀለም (መልክ) ይዞ ከትንሽ ጀምሮ የሚሰፋ መሆኑን ዶክተር ሱመያ አስገንዝበዋል። ለምሳሌ ይላሉ፤ ጉንጭ ላይ መውጣት ቢጀምር ወደ ሁለቱም ጉንጮች ከዚያም ወደ ግንባር እንዲሁም አገጭ እና አፍንጫ ሊደርስ እንደሚችል ገልጸዋል። በሂደትም የማቃጠል፣ የመቆጥቆጥ እና ማሳከክ ሁኔታ ሊኖረው እንደሚችል ነው ያነሱት። • ሕክምና መንስዔዎቹን ዐውቆ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ያስገነዘቡት ዶክተር ሱመያ፤ የፀሐይ ጨረር መከላከያዎችን መጠቀም፣ በሕክምና የሚሰጡ መድኃኒቶችን ሳያቋርጡ በትዕግስት መጨረስ (ቶሎ ለውጥ አላየሁበትም ብሎ አለማቋረጥ) እንደሚገባም መክረዋል። የማዲያት ሕክምና ስኬታማነቱ ለሁሉም ሰው በዕኩል ጊዜ እንደማይታይ በመግለጽ፤ እንደተከሰተበት ጊዜ ከሰው ሰው እንደሚለያይ በአጽኦት ተናግረዋል። ለምሳሌ አሉ፤ ዓመታት ያለፉት ማዲያት እና 2 ወራት የሆኑት ሕክምና እኩል ቢጀመርም በተመሳሳይ ጊዜ ላይድኑ እንደሚችሉ አመላክተዋል። ስለዚህ የሌላኛው ድኖ የኔ አልዳነም በሚል ሕክምናን ማቋረጥ ስህተት መሆኑንም ነው ያስረዱት። በሌላ በኩል ማዲያትን አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አረጋግጠው፤ ይህም የሚሆነው መንስዔዎቹን በማወቅ የማዲያት ተጋላጭ ባለመሆን ነው ብለዋል። ከተቻለ በየሥድስት ወሩ ወይም በየዓመቱ የቆዳ ጤና ምርመራ ማድረግ እና ያለበትን ደረጃ ማወቅም የሚከሰት ችግር ቢኖር እንኳ ሥር ሳይሰድድ በማከም ቶሎ እንዲድን ማድረግ ይቻላል ነው ያሉት።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 151
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ጤና ከሀገር በቀል ስኬት ወደ አህጉራዊ መሪነት
Apr 23, 2026 202
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ እያከናወነች ያለችው ስራ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂካዊ የሆኑ ተቋማዊና የፖሊሲ መሰረቶች ተጥለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መቋቋም ለሀገራዊ ችግሮች በቴክኖሎጂ የታገዘ መፍትሄ ለማግኘት ትልቅ አቅም የፈጠረ ሲሆን፣ ብሄራዊ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፖሊሲ ተቀርጾ መጽደቁ ደግሞ የዘርፉን ልማትና አጠቃቀም በተደራጀ መንገድ ለመምራት አስችሏል። እነዚህ እርምጃዎች ሀገሪቱ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እና 2030 ስትራቴጂ ውስጥ ቴክኖሎጂውን እንደ ቁልፍ የለውጥ አቅጣጫ እንድትጠቀም በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የቴክኖሎጂ ሽግግሩን ዘላቂ ለማድረግም በሰው ኃይል ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። በአሁኑ ወቅት አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በኮዲንግ፣ በዳታ ሳይንስ እና በክህሎት ለማሰልጠን የተጀመረው ግዙፍ ፕሮግራም የለውጡ አንቀሳቃሽ ኃይል እየሆነ ነው። ከዚህም ባለፈ፣ በአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ እንዲገነባ መታቀዱና በዚህ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባልነት ውስጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት እንዲሳተፍ መወሰኑ፣ ሀገሪቱ ቴክኖሎጂውን ለውሳኔ ጥራትና ለምርምር በከፍተኛ ደረጃ እየተጠቀመችበት መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ እንደገለጸው፣ ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በሹመት ደብዳቤው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ AI ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ ማድረጉ ተመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አክሎ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የAI አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል እና በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ለሀገራዊ ለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ በዝርዝር አስፍሯል። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የAI ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የተያዘው ሥራ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክርም ተገልጿል። ይህ አህጉራዊ እውቅና በተለይ በጤናው ዘርፍ የታዩ ውጤቶችን ያካትታል። ኢትዮጵያ በኤአይ የታገዘ ዲጂታል ኤክስሬይን ለሳንባ ነቀርሳ ምርመራ ካዋሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። በተጨማሪም የ"HEP Assist" መተግበሪያን በሙከራ ደረጃ በማስጀመር፣ በገጠር የሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ውስብስብ ምልክቶችን ሲያዩ ሙያዊ የሕክምና ውሳኔ እንዲሰጡ ድጋፍ እየተደረገ ነው። እነዚህ የዲጂታል ጤና ስራዎች በ7 ክልሎችና በ15 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ መጀመራቸው፣ ቴክኖሎጂው በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የአገልግሎት ልዩነት ለማጥበብ ያለውን ፋይዳ ያሳያል። በአጠቃላይ፣ የኤአይ ቴክኖሎጂ በጤናው ዘርፍ ከሚሰጠው የጡት ካንሰር፣ የአንጎል እብጠትና የቆዳ በሽታዎች ምርመራ ባለፈ፣ በግብርና፣ በፋይናንስና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥም በስፋት እየገባ ይገኛል። በ2030 በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ሆስፒታሎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል አገልግሎት ለመቀየር የተቀመጠው ግብ፣ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የጀመረችውን የቴክኖሎጂ ነጻነትና የመሪነት ጉዞ ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓት በጤና፣ በግብርና እና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በጤናው ዘርፍ እንደ ካንሰር እና ሳንባ ነቀርሳ ያሉ በሽታዎችን ቀድሞ በመለየት የህክምና ጥራትን ሲያሻሽል፣ በግብርናው ደግሞ የሰብል ተባዮችንና የቡና በሽታዎችን በመለየት ምርታማነትን እያሳደገ ነው። ከዚህ ባለፈም ቴክኖሎጂው በመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥ እና በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ሰፊ የመረጃ ትንታኔዎችን በፍጥነት በማከናወን፣ የሥራ ፍጥነትን እና የውሳኔ አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ ይገኛል። የዘርፉ ፋይዳ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባለፈ የሀገሪቱን የዲጂታል ሉዓላዊነት እና የሰው ኃይል አቅም በመገንባት ላይ ያተኩራል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶችን በኮዲንግ እና በዳታ ሳይንስ በማሰልጠን እንዲሁም የፈጠራ ማዕከላትን (Startups) በመገንባት፣ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በሌሎች ላይ ጥገኛ ከመሆን ወጥታ የራሷን የዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ይህም በአህጉር ደረጃ ለሚደረጉ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች እንደ አርአያ በመሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ ፍትሃዊነት የመጠቀም ጥቅል ፋይዳው የጎላ እንዲሆን አድርጎታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሹመት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ ያጎላል። በተጨማሪም ሹመቱ የኢትዮጵያ ተሞክሮ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ማግኘቱንና አፍሪካ በኃላፊነትና በፍትሐዊነት በታጀበ የኤአይ አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንድትሆን የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣም ያደርጋታል።
ኢትዮጵያ በአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ መንገድ
Apr 21, 2026 1445
(በዮሐንስ ደርበው) ታሪክ እንደሚነግረን፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥቅም ለመጀመሪያ ጊዜ ዕውቅና ያገኘው የኢንዱስትሪያዊ ንብረት ጥበቃን በሚመለከተው በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1883 በተፈረመው የፓሪስ ስምምነት እንዲሁም፤ በ1886 የተፈረመውን የሥነ-ጽሑፍና ሥነ-ጥበብ ሥራዎች ጥበቃን የተመለከተውን የበርን(ስዊዘርላንድ) ስምምነት ተከትሎ ነው። እነዚህ ስምምነቶችም በዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት የሚተዳደሩ መሆናቸው ይታወቃል። ኢትዮጵያ የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣንን፤ በ2022 ዓ.ም ፈጠራንና ኢኖቬሽንን በማበረታታት የፈጠራ ሐሳቦችን ወደ ዕሴት በመለወጥ ሂደት ለሀገራዊ ብልጽግና ቁልፍ ሚና የሚጫወት በአፍሪካ ተምሳሌት የአዕምሯዊ ንብረት ተቋም ለማድረግ እየታተረች ነው። ለዚህ ርዕይ መሳካትም፤ ተቋሙ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት ለሀገራዊ ፈጠራ መጎልበት፣ የኢኖቬሽን፣ ቴክኖሊጂ ሽግግር እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ማደግ ጥቅም ላይ የሚውልበትን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ሀገራዊ የመዋቅር ሽግግርን መደገፍ የሚል ተልዕኮ አንግቦ እየሠራ ይገኛል። የእስካሁኑ የንግድ ምልክት፣ ቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና የፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) ምዝገባ የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ወርቅነህ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ2015 ዓ.ም እስከ ያዝነው በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ድረስ በንግድ ምልክት፣ በቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና በፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) 20 ሺህ 476 ምዝገባዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ 14 ሺህ 729 የንግድ ምልክቶች፣ 5 ሺህ 254 የቅጅና ተዛማጅ መብቶች እንዲሁም 1 ሺህ 781 የፈጠራ ሥራ ባለቤትነት ምዝገባ በተቋማችን አማካኝነት ተከናውኗል። የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች ምንድን ናቸው? አዕምሯዊ ንብረት ማለት በሰው ልጅ አዕምሮ የሚፈጠሩ የፈጠራ ሥራዎችን የሚመለከት መሆኑን የገለፁት አቶ ብሩክ፤ እነዚህ የፈጠራ ሥራዎች እንደማንኛውም ቁሳዊ ሀብት በንብረትነት የሚታወቁበትን አግባብ የያዘው ሥርዓት ደግሞ የአዕምሯዊ ንብረት መብት እንደሚሰኝ ያስረዳሉ። በዚህ አግባብ፤ የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች እንደማንኛውም ቁሳዊ ንብረት ሁሉ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ባለመብቶች የሚሰጡ የባለቤትነት መብቶች መሆናቸውን እንረዳለን። ለዚህም እንደ ምክንያት የሚቀርበው እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፤ ወጥ ሥራዎችን ለማመንጨት የፈጠራ ባለመብቶች ዕውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውንና ጊዜያቸውን መስዋዕት በማድረግ ከብዙ ድካም በኋላ ያገኟቸው የፈጠራ ውጤቶች በመሆናቸው ነው። ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ ለምን አስፈለገ? አንድም፤ የሰው ልጅ ቀጣይ ዕድገትና የኑሮ ደኅንነት ዋስትና መሠረት የሚያርፈው በቴክኖሎጂና ባሕል ዘርፎች በሚያሳርፋቸው ፈጠራዊ ብቃቶቹ በመሆኑ እንዲሁም የምርምርና የፈጠራ ሥራዎችን ለማካሄድ ተጨማሪ ሀብት የሚያስገኝ በመሆኑና ይህም የኢኖቬሽን ሥርዓቱን ስለሚያሳድግ ነው ይላሉ አቶ ብሩክ። እንዲሁም፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃና ዘርፉን ለሕዝብ የማስተዋወቅ ተግባር ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በማረጋገጥ የድርሻውን ስለሚወጣና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት በአጠቃላይ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ በተሻለ ደረጃ ላይ እንዲቆም ስለሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም፤ ሀገራት ጠንካራ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠሩ ቁጥር ዘርፉ ለኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ የልማት መሣሪያ መሆኑን ይገነዘባሉ። ጠንካራና ፍትሐዊ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠራ ባለቤቶችና በተጠቃሚው ሕዝብ ዘንድ ሚዛናዊ ነው ያሉት አቶ ብሩክ። በአጠቃላይ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን በአጽነዖት አንስተዋል። ዜጎች በአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት እንዴት ተጠቃሚ ይሆናሉ? ባለብዙ ቢሊየን ዶላር የፊልምና ድምጽ ሪከርድስ አሳታሚዎችና ሶፍትዌር ኢንዱስትሪዎች ለብዙ ሚሊየኖች የመዝናኛ ሥራዎች የሚያበረክቱት የቅጅ መብት ጥበቃ በመኖሩ መሆኑን መገንዘብ እንደሚገባም አቶ ብሩክ ይናገራሉ። በሌላ በኩል ተጠቃሚዎች የሚፈልጓቸውን ምርቶችና አገልግሎቶችን መለየት የሚያስችላቸው ብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ የንግድ ምልክቶች ጥበቃና የመብት ማስከበር ሥርዓቶች ባይኖሩ ኖሮ ተመሳስለው በሚቀርቡ ምርቶችና አገልግሎቶች መታለልና ሌሎችም ችግሮች ያጋጥማቸው እንደነበርም ጠቁመዋል። ስለዚህ ምርቶችን በመሸመት ሂደትም በምርቶችና አገልግሎቶች ላይ ያለምንም ግራ መጋባት ግብይቱን ማከናወን እንደሚያስችላቸው መገንዘብ ይቻላል። እንደ አቶ ብሩክ ገለጻ፤ ለፓተንት የፈጠራ ሥራዎች ጥበቃ በመደረጉ መሰጠት የሚገባቸው ማበረታቻዎች የማይሰጡ ከሆነ፤ የፈጠራ ባለሙያዎች ቀጣይ የምርምር ሥራዎችን ማሳደግና ማስፋት እንደማይችሉ ይገመታል። በቀጣይነት የሚገኙ የተሻሻሉ የፈጠራ ሥራዎች አለመኖራቸው ደግሞ፤ በምርቶች ተጠቃሚና አጠቃላይ የኑሮ መሻሻል ሂደት ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተፅዕኖ ይኖረዋል። የአዕምሯዊ ንብረት ዓይነቶች እንዴት ይመደባሉ? የአዕምሯዊ ንብረት፤ የኢንዱስትሪያዊ ንብረት (Industrial Property) እና የቅጅና ተዛማጅ መብቶች (Copyright and Related Rights) በሚሉ ሁለት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚመደብ ያስረዳሉ። አክለውም፤ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት በውስጡ፤ የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ የኢንዱስትሪያዊ ንድፍ እና የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች የተሰኙ አራት ክፍሎችን እንደሚይዝ ያብራራሉ። ፓተንት ምንድን ነው?፡- ፓተንት ማለት በአንድ ቴክኒካዊ ባሕርይ ባለው የፈጠራ ሥራ ላይ የሚኖር የፈጠራ ባለቤትነት ብቸኛ መብት መሆኑን አቶ ብሩክ አስረድተዋል። የፓተንት መብት በአንድ ምርት (ለምሳሌ ማሽን ወይም የአመራረት ሂደት (Process) ሊሰጥ የሚችል ሲሆን፤ ፈጠራውም ለአንድ ቴክኒካዊ ችግር መፍትሔ የሚያስገኝ መሆን ይኖርበታል ይላሉ። ከፈጠራ ሥራው አመንጪ ይሁንታ ውጭ ሥራውን ገበያ ላይ ማዋል፣ መጠቀም፣ ማሰራጨት፣ መሸጥ ወዘተ… እንደማይቻልም አክለዋል። ፓተንት ለባለ መብቱ የጥበቃ መብት የሚያስገኝ ሲሆን፤ የጥበቃው ዘመንም በአጠቃላይ እስከ 20 ዓመት ሊደርስ ይችላል። ፓተንት የሚያስገኛቸው ሕጋዊ (የጥበቃ) መብቶች፡- የፈጠራ ሥራውን መጠቀም የሚችሉና የማይችሉ ሰዎችን መወሰን፤ ሦስተኛ ወገኖች ሥራውን እንዲጠቀሙ የመፍቀድ ወይም የፈቃድ ውል ስምምነት የመስጠት እንዲሁም የፈጠራ ሥራውን የመሸጥ (ለአዲስ የፓተንት ባለመብት) የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል ሥራ አስፈጻሚው። የፓተንት ሥራዎች ለምን ያስፈልጋሉ?፡- ይህን ሲያብራሩም፤ ፓተንት ለፈጠራ ባለመብቶች ዕውቅናንና ሽልማቶችን (ማበረታቻዎችን) የሚሰጥ በመሆኑ፣ ፈጠራዎቹ የኢኖቬሽን ሥራዎችን ስለሚያጠናክሩና በዚህም ቀጣይነት ያለው የሰው ልጅ ሕይወት መሻሻልን የሚያረጋግጥ በመሆኑ እና በሌሎችም በጎ አስተዋጽዖዎች ፓተንት በዕጅጉ አስፈላጊ ነው ብለዋል። የንግድ ምልክት ምንድን ነው?፡- የንግድ ምልክት ማለት አንድን ምርት ወይም አገልግሎት ከሌላው ምርትና አገልግሎት እንዲለይ ለማስቻል በንግድ ምልክት ባለቤቶች ለምርታቸውና አገልግሎታቸው መለያ እንዲሆን ጥቅም ላይ የሚውል ልዩ ምልክት መሆኑን ተናግረዋል። የንግድ ምልክት ሸማቹ ሕብረተሰብ የሚፈልገውን ምርትና አገልግሎት በቀላሉ ለይቶ እንዲገዛ ከማስቻሉም በላይ በሚገዛው ምርትና አገልግሎት ጥራት ላይ በመተማመን ፍላጎቱን እንዲያሟላ ያደርጋል። የንግድ ምልክት ለባለመብቱ ምን ጥቅም ያስገኛል?፡- ምርቶቹ (አገልግሎቶቹ) በተጠቃሚዎች እንዲለዩለት ወይም እንዲታወቁለት ያደርጋል፣ ክፍያን መሠረት አድርጎ ሦስተኛ ወገን እንዲጠቀምበት የመፍቀድ፣ የንግድ ምልክቶች በራሳቸው ዋጋ አላቸው (የአዕምሯዊ ንብረት ዋጋ ትመና (IP Valuation) ለምሳሌ በፈረንጆቹ በ2026 የመጀመሪያ ወራት አፕል (Apple) 600 ቢሊየን ዶላር፣ ማይክሮሶፍት (Microsoft) 565 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር፣ ጉግል (Google) 433 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ዋጋ ግምት እንደነበራቸው ተብራርቷል። በተጨማሪም፤ የንግድ ምልክት በሕግ በሚቀመጥ የጊዜ ገደብ መሠረት እየታደሠ ለዘላለም ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል፤ የንግድ ምልክት ባለቤቱን በማስተዋወቅ ዕውቅናና የገንዘብ ትርፍን ያስገኛል፤ የንግድ ምልክት ተገቢ ያልሆኑ የንግድ ውድድሮችን በመግታት ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል (ተመሳስለው የሚሠሩና ለገበያ የሚቀርቡ ሥራዎችን (Counterfieited Products) ለመዋጋት ዓይነተኛ መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል፤ የንግድ ምልክት ሰዎች ምርቶቻቸውንና አገልግሎቶቻቸውን ሚዛናዊ በሆነ አግባብ እንዲያቀርቡ በማድረግና በብሔራዊና ዓለም አቀፍ ደረጃ የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት እንዲኖር ምቹ ሁኔታ በመፍጠር አስተዋጽዖው የላቀ ነው ብለዋል። ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ምንድን ነው?፡- ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ በምርቶች ሥነ-ውበት (Esthetics) ላይ ተመስርቶ ቅርጽን፣ መስመሮችን ወይም ቀለምን በመጠቀም ለገበያ የሚቀርቡ ምርቶች የገዥዎችን (ሸማቾችን) ቀልብ ለመሳብ እንዲችሉ በምርቶች ላይ የሚገለጽ የንድፍ ጥበብ ዘርፍ ነው ያሉት አቶ ብሩክ፤ ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች በኢንዱስትሪና ዕደ-ጥበብ ምርቶች ላይ ተዘጋጅተው ሊወጡና ለገበያ ሊቀርቡ ይችላሉ ይላሉ። ዘርፉ ከቴክኒካልና ሕክምና መሣሪያዎች አንስቶ እንደ ሠዓት፣ ጌጣጌጦችና ሌሎች የቅንጦት ምርቶች ዕቃዎችን ሊያካትት ይችላልም ብለዋል። የቤት ዕቃዎችን፣ የኤሌክትሪክ መሣሪያዎችን፣ ተሽከርካሪዎችና የሕንጻ ንድፎችን እንዲሁም የጨርቃጨርቅ ንድፍ ውጤቶች በኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ሥር የሚወድቁ ይሆናሉ ይላሉ። ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች ጥበቃ የሚደረግላቸው አዲስ ወይም ወጥ ከሆኑ ብቻ መሆኑን ገልጸው፤ በዲዛይኑ ውስጥ ከሚገለጸው ምርት ጋር ተያያዥ የሆኑ የቴክኒክ ጉዳዮች ጥበቃ እንደማይደረግላቸው አስታውቀዋል። ለኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ጥበቃ ማድረግ ለምን ያስፈልጋል?፡- በምርቶች ውበት ላይ የሚገለጽ በመሆኑ የተጠቃሚውን ዐይን ይስባል፣ የምርቶችን ዋጋ ይጨምራል፣ ፈጠራንና ውድድርን ያበረታታል፣ ለባለመብቱ ብቸኛ መብትን ያጎናጽፋል፣ በኢንዱስትሪዎች፣ ባሕላዊ ጥበብና በዕደ ጥበብ ዘርፍ ፈጠራ በማሻሻል ኢኮኖሚ እንዲያድግ ያደርጋል፣ የወጭ ንግድን (Export Trade) ያሳድጋል በማለት የኢንዱስትሪ ንድፍ ጥበቃ አስፈላጊነትን ያብራራሉ። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካች ምንድን ነው?፡- የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች በምርቶች ላይ የሚቀርቡ ምልክቶች ሆነው እነዚህ ምልክቶች አንድ የተወሰነ አካባቢን በምርቱ ምንጭነት የሚያመላክቱና ጥራትንና ዝናን ከቦታው ጋር አስተሳስረው የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን አቶ ብሩክ ያስረዳሉ። በአብዛኛው የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች ልዩ ምርቱ የሚገኝበትን የቦታ ስም (Specific Local Geographyical Factors – Climate, Soil) ይይዛሉ። ለምሳሌ፡- Roquefort for Cheese -France፣ የማረቆ በርበሬ፣ የሸኖ ቅቤ፣ የዓድኣ ጤፍ … የመሳሰሉት ምርቶች ተጠቃሾች ናቸው። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾችን መጠበቅ ለምን ያስፈልጋል?፡- ተጠቃሚዎች ምርቶች የሚገኙበትን ሀገር ወይም አካባቢ በቀላሉ ለመለየት፣ ሕጋዊነት በሌላቸው ወገኖች የምርቱ መገኛ አካባቢ እና የምርቱ ዝና በተሳሳተ መልኩ ለሌላ ምርት መጠሪያ እንዳይውል ለመከላከል ይረዳል ይላሉ። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምንድን ናቸው?፡- የቅጅ መብት በሥነ-ጽሑፍ እና ሥነ-ጥበብ ዘርፍ ወጥ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ደራስያን፣ አርቲስቶች ወዘተ… የባለቤትነት መብት የሚሰጥ የሕግ ማዕቀፍ መሆኑንም ነው ሥራ አስፈጻሚው የሚያስረዱት። በአንጻሩ ተዛማጅ የቅጅ መብት ማለት ይላሉ አቶ ብሩክ፤ በወጥ የፈጠራ ሥራዎች ላይ ተመስርተው የሚሠሩ ተዛማጅ (Related) የፈጠራ ሥራዎችን ያካትታል። ለምሳሌ፡- ከዋኞቹ (ተዋንያን እና ዘፋኞች)፣ ድምጽ ሪከርዲንግስ፣ አሳታሚዎች (ኮምፓክት ዲስኮች)፣ የብሮድካስት ተቋማት፣ (ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን) የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ ሲሉ ዘርዝረዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምን ዓይነት መብቶች ያስገኛሉ?፡- ባለመብቶች ሥራዎቻቸውን ለመጠቀም ወይም ሦስተኛ ወገኖች እንዲጠቀሙባቸው የመፍቀድ፣ ሥራዎች እንዲባዙ፣ ለሕዝብ እንዲዳረሱ፣ እንዲሠራጩ፣ እንዲተረጎሙ ወይም ወደሌላ ሥራ እንዲቀየሩ የመፍቀድ ወይም የመከልከል፣ የደራሲነት (የአመንጭነት) መብት ዕውቅና እንዲያገኙ፣ በብዕር ስም የመጠቀም መብት፣ ክብሩንና መልካም ስሙን የሚያጎድፍ የሥራ መዛባት እንዳይኖር የመጠበቅ ወይም የሥራው ወደሌላ መቀየር የሚያስከትለውን ጉዳት የመቃወም ወዘተ መብቶችን ያስገኛሉ ብለዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ምን ጥቅሞች ያስገኛል?፡- የሰውን ልጅ የፈጠራና ኢኖቬሽን ጥረቶችን ያሳድጋል፣ ለፈጠራ አመንጭዎች መበረታታትን ይፈጥራል፣ የሕጋዊ ተፈጻሚነትን በማረጋገጥ አመንጭዎችና በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች መዋዕለ-ነዋይ እንዲያፈሱ የፈጠራ ሥራዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚኖራቸውን የሥርጭት ሽፋን ያሳድጋል ነው ያሉት አቶ ብሩክ። የፓሪስ ስምምነት አባል ኢትዮጵያ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር ለመሆን ለዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት (WIPO) ያስገባችው ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስምምነቱን ነሐሴ 9 ቀን 2017 ዓ.ም በማጽደቁ ከዚሁ ዕለት ጀምሮ ለስምምነቱ ተገዢ ሆናለች። አቶ ብሩክ እንዳብራሩት፤ የፓሪስ ስምምነት በጥቅሉ የኢንዱስትሪያዊ ንብረቶችን ጥበቃ የሚመለከት ነው። የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ፣ የግልጋሎት ሞዴል (በአንዳንድ ሀገራት ሕግ ኢትዮጵያን ጨምሮ “የአነስተኛ ፈጠራ የባለቤትነት መብት” በመባል የተደነገገ)፣ የአገልግሎት ምልክት፣ የንግድ ስም (የኢንዱስትሪ ወይም የንግድ እንቅስቃሴ የሚካሄድባቸው ስያሜዎች)፣ ጂኦግራፊያዊ አመላካች እና ፍትሐዊ ያልሆነ ውድድርን መከላከል ያካተተ ነው። የስምምነቱ መሠረታዊ ድንጋጌዎች በሦስት ዋና ዋና መርሆዎች እንደሚከፈሉ ጠቁመው፤ እነሱም፡- የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር መሆን በሌሎች አባል ሀገራት ውስጥ እንደ ዜጋ የመስተናገድ መብት፣ የቀዳሚነት መብት የማግኘት፣ በቀላሉ ዓለም አቀፍ ጥበቃ የማግኘት አሠራር እና መሰል ጉልህ ጥቅሞችን የማግኘት ዕድል ይሰጣል ሲሉ ይገልጻሉ። በመሠረቱ የፓሪስ ስምምነት የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃን በማቀላጠፍ አዳዲስ ግኝቶችንና ፈጠራዎችን እንዲሁም የንግድ ሥራዎች ድንበር ሳይገድባቸው የፓተንትና የንግድ ምልክት መብቶች በቀላሉ እንዲጠበቁ በማድረግ ፈጠራን፣ ንግድን እና ኢኮኖሚያዊ እድገትን እውን ያደርጋል ብለዋል። የዘንድሮው የአዕምሯዊ ንብረት ቀን የፊታችን ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም “አዕምሯዊ ንብረትና ስፖርት፤ እንዘጋጅ፣ እንጀምር፣ እንፍጠር!” በሚል መሪ ሐሳብ ዓለም አቀፉ የአዕምሯዊ ንብረት ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል። በስፖርት ዓለም ውስጥ የሚከሰቱ ተወዳዳሪዎች የግልና የጋራ ፈጠራዎች፣ ንድፎች፣ ብራንዶችና የመልካም ዝና ታሪኮችን ለመጠበቅና ሀገራትን ጭምር ለማስተዋወቅ የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃ ሥርዓት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል። ምክንያቱም ስፖርት በባሕርይው በውድድር ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን፤ ከሀገራት ዝና፣ ከፋሽን ዲዛይን፣ ከመዝናኛ፣ ከሚዲያ ሥርጭት፣ ከጤናና ከዕለት ተዕለት መገልገያ ቁሶች ጋር የሚገናኝ በመሆኑ ነው።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 18, 2026 958
ከሚያዝያ 5 እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ በንፋስ ኃይል አማካኝነት ጨለማን ለመግፈፍ፣ ዐቅምን በለየ የቅድመ ጥናት እና ልዩ ዕቅድ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ዕውን አድርጋለች ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት 100 ሜጋ ዋት ንጹህ የኃይል አቅርቦት በመጨመር ወደ ዘርፈ-ብዙ እና ቀጣይነት ባለው የኃይል መጻዒ ዕጣ ፈንታ ለመገንባት የምናደርገውን ጉዞ ያጠናክረዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ አብነት ነው ብለዋል በወቅቱ። በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል፤ ከምንጊዜውም በላይ ታላቅ የምንሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉም አመላክተዋል። • ከኮፕ32 አስተናጋጅነት ጋር በተያያዘ ምክክር መደረጉ የኮፕ32 አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ መጀመሯን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል ሲሉ ገልጸዋል። ከግምገማ ባሻገር የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልኅቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው ብለዋል። • የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከዚያም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይትም፤ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በቅኝ ያልተገዙ፣ ለአኅጉሩ ነፃነትና አንድነት ድምፅ በመሆን ከጋራ የጽናት ታሪክ የሚመነጭ ጥልቅና ዘመናትን የተሻገረ ግንኙነት አላቸው ያሉት ጠላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም እንደ ሁሌው ኢትዮጵያ ከሰፊ ገበታዋ ያላትን ታላቅ ዐቅምና ዘላቂ ወዳጅነት አብረዋት ለሚጓዙ ሁሉ ለማካፈል ዝግጁ ናት ብለዋል። ጉብኝቱም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን የቆየ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለማስፋት ወሳኝ ምዕራፍን ከፍቷል ሲሉ ገልጸዋል። ከሁለትዮሽ ስብሰባው በመቀጠልም በሁለቱ ሀገራት በኩል ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጉዞ ያካበተችውን ልምድ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማካፈል እንዲሁም ከአጋሮቻችን የተለያዩ ዕይታዎችን በመቅሰም ለአኅጉሩ ዕድገት ዘላቂና አፍሪካዊ መፍትሔዎችን በጋራ ለማፍለቅ እንደ ወሳኝ መሠረት ያገለግላሉ ነው ያሉት። • የፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ባሳለፍነው ሳምንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ቀጣይ ትብብሮችን በምናጠናክርባቸው ቁልፍ መስኮች ላይ መክረናል ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም፤ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ፣ የተሻገረ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ በበቂ ሁኔታ ዜጎችን ሥራ ለማስያዝ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሚና አይተኬ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሥራ ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚ ያሸጋግራል፣ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሻገር እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ያገለግላል በማለት አብራርተዋል። በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነት አንዱ አንጓ ነው በማለት አስረድተዋል። የብዙ መንግሥታትና የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል። አክለውም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል። አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል። እንዲሁም የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግሥት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አብራርተዋል። ከተማ አያስፈልግኝም፤ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አመላክተዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በወሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገራችን በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ሥር እየሰደደ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሐሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል። እንዲሁም በ "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ሥራ ማስጀመራቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ማሳያ እና የወሎ የብልጽግና ተስፋ ነው ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የ"መደመር" ዕሳቤ በተግባር የታየበት፣ የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለ ሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት ነው ሲሉም ገልጸል። ያየነው ልማት የሰላም ውጤት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ በማለት፤ በአንድነት እና በትጋት ከሠራን ይህ ቀጣና የዕድገትና ብልጽግና መዳረሻ መሆኑ አይቀሬ ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንትን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት መሠረተ-ልማት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ግብዓቶችን በማመላለስ የኢኮኖሚያችን የደም ሥር፣ የብልጽግናችን መሠረት ነው ብለዋል። በዐውደ ርዕዩ የተመለከትነውም ወሳኝ የልማት ተቋሞቻችን፣ መሠረተ-ልማትን እንደ ሀገር በቅንጅትና በትብብር የመምራት አዲስ የሥራ ባህል እየገነቡ መሆናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግሥት በመንገድ፣ በኃይል፣ በመስኖ፣ በባቡርና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፍ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚሠራውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። አሁን ያለንበት ወቅት የሥራ፣ የውጤት እና የተስፋ ዘመን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ትናንት የተገነባው ለዛሬ፣ ዛሬ የምንገነባው ደግሞ ለነገው ትውልድ ኩራት እና የብልጽግና ዋስትና ነው ብለዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3922
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2675
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8462
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6950
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 167
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 548
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።