ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራዎች የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት እንዲረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው
Jul 12, 2025 13
አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በሀገሪቱ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢንሼቲቭ ሥራዎች የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት እንዲረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ በብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ገለጹ። የፌደራል እና የክልሎች የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊዎች ዛሬ በአርባ ምንጭ ጋንታ ተራራ ላይ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። በዚሁ ጊዜ በብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) እንደገለጹት በሀገራችን ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢንሼቲቭ ሥራዎች የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት እንዲረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። የአረንጓዴ ልማት ሥራው የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ፣ የከርሰ ምድር ውሃን በማጎልበትና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ነው ያሉት። በአርባ ምንጭ ጋንታ ተራራ ላይ ከአካባቢው አመራሮችና ነዋሪዎች ጋር በመሆን አረንጓዴ ዐሻራ በማኖራቸው መደሰታቸውን ገልጸው በዚህም ችግኝ ብቻ ሳይሆን የአንድነት፣ የአብሮነት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነትን ትርክት ጭምር ተክለናል ብለዋል። የተተከሉ ችግኞች አርባ ምንጭ ከተማን ከጎርፍ ከመታደግ ባለፈ ዓባያና ጫሞ ሐይቆችን ከደለል በመከላከል ለሐይቆች ህልውና ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ገልጸዋል። በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ሳሙኤል ኡቦያ በበኩላቸው የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት በክልላቸው የአካባቢን ስነ-ምህዳርና ብዝሃ ህይወት በመጠበቅ ጉልህ ጠቀሜታ እያስገኘ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአርባ ምንጭ ጋንታ ተራራ ላይ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጋራ የአረንጓዴ ዐሻራ ማኖራቸው አብሮነትን እንደሚያጠናክር ገልጸዋል። በብልጽግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ አሚና ኢብራሂም፣ የአረንጓዴ ዐሻራ የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ለማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ በአርባ ምንጭ ከተማ ጋንታ ተራራ ላይ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ዐሻራቸውን ማኖራቸው ይህንኑ የሚያጠናክር ነው ብለዋል። የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ(ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ ከተጀመረ ወዲህ የዞኑ የደን ሽፋን እንዲሁም ምርትና ምርታማነት እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። ዛሬ የተተከሉ ችግኞች ለአርባ ምንጭ ከተማ ህልውና ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኙ በመሆኑ በቀጣይ ህብረተሰቡን በማስተባበር እንደሚንከባከቡ ገልጸዋል። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት በአርባ ምንጭ ከተማ ዶይሳ ቀበሌ የአቅመ ደካማ እናት መኖሪያ ቤትን ሙሉ ወጪ በመሸፈን ዛሬ በአዲስ መልክ ግንባታ አስጀምሯል። የብልጽግና ፓርቲ ዋናው ጽህፈት ቤት የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ላይ በአርባ ምንጭ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል።
የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ
Jul 12, 2025 14
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ ሶስተኛ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ። ከምሽቱ 4 ላይ አዘጋጇ ሞሮኮ ከሴኔጋል በፕሪስን ሙላይ አብደላ ስታዲየም ይጫወታሉ። በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ዛምቢያ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኤል ባቺር ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ሞሮኮ አራት ነጥብ በመያዝ ምድቡን በአራት ነጥብ እየመራች ትገኛለች። ሴኔጋል በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛለች። አዘጋጅ ሀገር ሞሮኮ ማሸነፍ ወይም አቻ መውጣት ወደ ሩብ ፍጻሜው ያሳልፋታል። ተሸንፋም ጥሩ ሶስተኛ ሆኖ የማለፍ እድል አላት። ሴኔጋል ካሸነፈች በቀጥታ ሩብ ፍጻሜውን ትቀላቀላለች። አቻ መውጣት ወይም መሸነፍ ሁለተኛ አሊያም ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ እንድታልፍ ሊያደርጋት ይችላል። ዛምቢያ በምድቡ አራት ነጥብ በመሰብሰብ ተመሳሳይ ነጥብ ባላት አዘጋጇ ሞሮኮ በግብ ክፍያ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። ማሸነፍ ዛምቢያ የማንንም ውጤት ሳትጠብቅ ወደ ሩብ ፍጻሜ እንድትገባ ያስችላታል። ተሸንፋ ወይም አቻ ወጥታ በሂሳባዊ ስሌት ቀጣዩን ዙር የመቀላቀል እድል ልታገኝ ትችላለች። ሁለት ሽንፈት ያስተናገደችው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛለች። ማሸነፍ የኮንጎን ምርጥ ሶስተኛ ሆና የማለፍ እድሏን ሊያለመልመው ይችላል።
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መደጋገፍንና አብሮነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ ይከናወናል
Jul 12, 2025 20
አበሽጌ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፡- የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መደጋገፍንና አብሮነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከናወን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሀላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አለምፀሐይ ጳውሎስ ገለጹ። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እና ተጠሪ ተቋማት በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብርን ዛሬ አስጀምረዋል። በዚህ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሀላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አለምፀሐይ ጳውሎስ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መደጋገፍንና አብሮነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ ይከናወናል ብለዋል። በወረዳው ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተለያዩ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት እንደሚከናወኑም ተናግረዋል። ከሚከናወኑት ተግባራት መካከል 15 የአቅመ ደካማ ወገኖች መኖሪያ ቤቶችና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ እንዲሁም የችግረኛ ቤተሰብ አባላት ለሆኑ ለ2ሺህ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶች ድጋፍ እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል። በተጨማሪም የኮሪደር መንደር እንደሚገነባ ያመለከቱት ሀላፊ ሚኒስትሯ አትክልት እና ፍራፍሬ ልማትን ጨምሮ ሕብረተሰቡን በተለይም ወጣቱን በማሳተፍ የማስፋፋት ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል። በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ በተጀመረው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እና ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የጉራጌ ዞን ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
የመዲናዋ የ2018 በጀት 350 ነጥብ 13 ቢሊዮን ብር ሆኖ ጸደቀ
Jul 12, 2025 29
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የመዲናዋን የ2018 በጀት 350 ነጥብ 13 ቢሊዮን ብር አድርጎ አጸደቀ፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂዷል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ አብዱልቃድር ሬድዋን፥ የከተማ አስተዳደሩን የ2018 በጀት ዓመት ዝርዝር ረቂቅ በጀት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። ለ2018 በጀት ዓመት 350 ነጥብ 13 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን ገልጸው፥ በጀቱ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ108 ቢሊየን ብር ወይም የ45 በመቶ እድገት እንዳለው ገልጸዋል። ከአጠቃላዩ በጀት ለመደበኛ ወጪ 91 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር፣ ለካፒታል ሥራዎች 246 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲሆን ቀሪው 12 ቢሊዮን ብር ለመጠባበቂያ መሆኑን አብራርተዋል። የካፒታል በጀት ከፍ እንዲል የተደረገው ለሰው ተኮር ሥራዎች፣ ለቤት ልማት፣ ለኮሪደር ልማት እና ለከተማ አስተዳደሩ ወሳኝ ፕሮጀክቶች ትኩረት መስጠት በማስፈለጉ መሆኑን አንስተዋል። በጀቱ የከተማዋን ራዕይ፣ በሒደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችንና አዳዲስ የልማት ፍላጎቶችን፣ የታቀዱ አስተዳደራዊ ማሻሻያዎችን፣ አገልግሎት የማዘመን ስራን በፍጥነትና በውጤታማነት ለመተግበር ታሳቢ በማድረግ መዘጋጀቱን አስረድተዋል፡፡ ከአጠቃላይ በጀቱ ከ238 ቢሊየን ብር በላይ የሚሆነው ከታክስ፣ ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ከ56 ቢሊየን ብር በላይ፣ ታክስ ካልሆነ ገቢ ከ46 ቢሊየን ብር በላይ፣ ከመንገድ ፈንድ 1.8 ቢሊየን፣ ከውጭ ብድርና እርዳታ 6 ነጥብ 98 ቢሊየን ብር እንደሚሰበሰብ ጠቅሰዋል። የምክር ቤቱ አባላትም በረቂቅ በጀቱ ላይ በመወያየት በሙሉ ድምጽ አጽድቀውታል።
ዩኒቨርሲቲው ዘመናዊ የሠራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ የሚያጠናክሩ ብቁ ሙያተኞች እያፈራ ነው - ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር)
Jul 12, 2025 20
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ የሚያጠናክሩ ብቃትና ሥነ-ምግባር ያላቸው ሙያተኞች እያፈራ እንደሚገኝ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ፣ በቢዝነስ እና በኃብት አስተዳደር እንዲሁም በሌሎች የትምህርት መርኃ ግብሮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የዛሬው ተመራቂዎች ኢትዮጵያ በየዘመኑ ጀግኖችን የምታፈራ ሀገር ለመሆኗ ትልቅ ማሣያ ናችሁ ብለዋል። የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ የሰለጠነ የሠራዊት አባላትንና ሲቪል አመራር በማፍራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው በዚህም በእውቀት፣ በዓላማና በሙያዊ ልህቀት የታነጹ ሙያተኞችን እያፈራ ይገኛል ብለዋል። የሠራዊቱን የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ብቃት ለማላቅ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይም ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ ማገዝ የሚችሉ ብቁና ሥነ-ምግባር ያላቸውን ሙያተኞች እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል። በሌላ መልኩም በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም ሚኒስትሯ ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው ለሀገርና ለመጪው ትውልድ የሚሻገር ስራ መሥራቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል። ተመራቂዎች በታማኝነት፣ በቅንነትና በስነምግባር ሀገራቸውን ማገልገል እንዳለባቸው በአፅንኦት ተናግረዋል። በምርቃት መርኃ ግብሩ ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ሽልማት ተበርክቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በ2025 ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
ፖለቲካ
የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ብቁ ሰራዊት ከመገንባት በተጓዳኝ ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎችን እየፈጠረ ነው - ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ
Jul 12, 2025 64
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ብቁ ሰራዊት ከመገንባት በተጓዳኝ ዘመኑን የዋጁ ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች እየፈጠረ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ ገለጹ። ዩኒቨርሲቲው በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ፣ በቢዝነስ፣ በኃብት አስተዳደር እና በሌሎች የትምህርት መርኃ ግብሮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ፤ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ወታደራዊ፣ ሲቪል እና የጎረቤት ሀገራት ተማሪዎችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል ብለዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲው በእውቀትና በክህሎት ብቁ የሆነ የሰው ኃይል እያፈራ መሆኑንም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የመከላከያ ሰራዊቱን የተልዕኮ አፈጻጸም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርሱ ወታደራዊና ሲቪል አመራሮችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ ሀገርን የሚያሻግሩ ሥራዎች በመስራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው የመከላከያን የሰለጠነ የሰራዊት ግንባታ በማገዝ ላይ መሆኑንም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የሰራዊቱን ስምና ዝና በሚመጥን መልኩ የተዋቀረ ሲሆን ከመማር ማስተማር ስራዎች በተጓዳኝ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ስራዎችና ሌሎች ህብረተሰቡን የሚጠቅሙ ተግባራት እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ዘመናዊ ሰራዊት ለመገንባት ከውጭ የምታስገባቸውን ቴክኖሎጂዎች በሀገር ውስጥ ለመተካት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ስራዎችን በመሥራት ላይ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። ተመራቂዎች ባገኙት እውቀትና ከፍተኛ ክህሎት ሀገራቸውን በብቃት ማገልገል እንደሚገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በ2025 ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 122
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው በተሻሻለው የኢትዮጵያ ምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። አዋጁ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚቀርብ ማንኛውም ቅሬታ በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት የሚደነግግ ሲሆን የምርጫ ክልል አቤቱታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት ከዚህ በፊት ከህብረተሰቡ ይመደብ የነበረው ቀርቶ ቦርዱ አሰልጥኖ በሚመድባቸው የምርጫ አስፈጻሚዎች እንዲተኩ የሚያደርግ ነው። ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ አንድ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመመዝገብ የሚመለምለው አባል ከ5 ክልሎች የነበረ ሲሆን በተሻሻለው አዋጅ አንድ ፓርቲ አባላትን መመልመል ያለበት ከ7 ክልሎች ሊሆን እንደሚገባም በአዋጁ ተመላክቷል። አንድ ፓርቲ ከመንግሥት ድጋፍ ለማግኘት ከ30 በመቶ ከሚሆነው አባሉ የአባልነት መዋጮ መሰብሰብ እንደቅደመ ሁኔታም ተቀምጧል። በአዋጁ መሰረት ጥሰት ፈጽመው የተገኙ ፓርቲዎች እስከ አምስት ዓመት ድረስ ሊታገዱ የሚችሉበት ድንጋጌም ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል ነው። በውይይቱ ከተሳተፉ መካከል የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ በምርጫ ጣቢያ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አይቶ ውሳኔ ይሰጣል የሚለው የአንቀጹ ክፍል ለአተገባበር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል ብለዋል። የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ ባንዲራ በላቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲዎች 30 በመቶ መዋጮ እንዲያሰባስቡ የተቀመጠው ድንጋጌ ከነባራዊ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ወይ የሚለው ሊጤን እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው በአዋጁ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ድንጋጌዎች ሊካተቱ ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሌ በሰጡት ማብራሪያ በአዋጁ ፓርቲዎች 30 በመቶ ያህል መዋጮ ከአባላት ሊሰበሰቡ እንደሚገባ የተደነገገው ፓርቲዎች በመንግሥት በጀት ላይ ብቻ እንዳይመሰረቱና ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። አዋጁ አካል ጉዳተኞችንና ሴቶችን አካታች በሆነና ተሳትፏቸውን በሚያሳድግ መልኩ መቃኘቱን አንስተዋል። የመንግሥት ሰራተኞች በምርጫ ውድድር ወቅት ደሞዛቸውን ይዘው እንዲሳተፉ መደረጉ ለፖለቲካ ምህዳሩ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ነዋይ በሰጡት ማብራሪያ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚነሱ ቅሬታዎች በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ እንዲፈታ አቅጣጫ የተቀመጠው ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታልሞ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲያም ሆኖ ቅሬታዬ አልተፈታም የሚል ማንኛውም አካል ጥያቄውን በየደረጃው የሚያቀርብበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራ አንደሞ በበኩላቸው በህዝባዊ የውይይት መድረኩ የተነሱ ሀሳቦች ለአዋጁ ውሳኔ ሀሳብ የሚረዱ ግበዓቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር ላይ የፓርቲዎች ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በበኩላቸው ፓርቲዎች የወጣቶችን፣ የአካል ጉዳተኞችንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የበለጠ ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአባልነት መዋጮን በተመለከተም ፓርቲዎች አባላቶቻቸውን ሊያበረታቱ እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን ስራ ላይ ለማዋል የጀመራቸውን ተግባራት ሊያጠናክር እንደሚገባ ጠቁመው ፓርቲዎችም ይሄንኑ ስራ ሊደግፉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት ይሰራል - አቶ ፍቃዱ ተሰማ
Jul 11, 2025 81
ጎንደር፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ። ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የተውጣጡ የፓርቲው የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች የተሳተፉበትና በጎንደር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የግምገማ መድረክ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ማምሻውን ተጠናቋል። አቶ ፍቃዱ ተሰማ የግምገማ መድረኩ ማጠቃለያን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ ፓርቲው መጪው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን መላ አባላቱን የማዘጋጀት ስራዎቹን በትኩረት ያከናውናል ብለዋል። ለዚህም የአባላት የስነ-ምግባር ደንቦችን በማዘጋጀት በምርጫው የትብብርና ፉክክር ዴሞክራሲያዊ ባህል እንዲዳብር እንደሚሰራም ተናግረዋል። አባላቱ በፓርቲው እሳቤዎች፣ መተዳደሪያ ደንብና አሰራሮች ዙሪያ ወጥና የተቀራረበ ግንዛቤ በመያዝ ተቋማዊ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ አቅማቸውን የመገንባት ስራ ይከናወናል ብለዋል። የፓርቲው አደረጃጀቶች በልማት በሠላምና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል እንደሚሰሩም ጠቁመዋል። የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደፓርቲና መንግስት ሰፋ ያሉ ውጤቶች የተመዘገቡበትና የማንሰራራት ዘመን በተጨባጭ የታየበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዓመቱ በፓርቲው ውስጥ የአመለካከት፣ የተግባር አንድነትና ህብረ ብሔራዊነት የተጠናከረበት እንደነበርም ተናግረዋል። ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚደረገው ጥረት በጎ ጅምር የታየበት፣ ኢኮኖሚያዊ እድገቱ የሀገሪቱን በጀት በትሪሊዮን እንዲጸድቅ ያስቻለና የእዳ ቅነሳ የተደረገበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራና የከተሞች ኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤታማ እንደነበርም አብራርተዋል፡፡ በሠላም ማስከበር ሂደቱ የታጠቁ ኃይሎች የመንግስትን የሠላም አማራጭ ተቀብለው ተሃድሶ በመውሰድ በስፋት ወደ ሠላማዊ ህይወት መመለሳቸውንም አስታውሰዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳካ ፓርቲው የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ኃላፊው አረጋግጠዋል።
የከተማዋን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ተሳትፏቸውን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል
Jul 11, 2025 44
ወልዲያ ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፡- የወልዲያ ከተማን ሰላም አፅንቶ በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ተሳትፏቸውን ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ገለጹ። የከተማ አስተዳደሩ ከከተማው ወጣቶች ጋር በሰላምና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የምክክር መድረክ ዛሬ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ እንዳሉት፤ የአካባቢን ሠላም ለማፅናት ወጣቱ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የድርሻውን ሲወጣ ቆይቷል። በዚህም የህግ የበላይነትን በማስከበር ሰላም ማስፈን መቻሉን ገልጸው፤ የተገኘውን ሰላም አስጠብቆ ዘላቂ ለማድረግ ወጣቶች ሲያበረክቱ የቆዩትን አስተዋጽኦ ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። በሰሜን ምስራቅ ዕዝ የ801ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ዘውዱ ሰጥአርጌ በበኩላቸው፤ የመከላከያ ሰራዊቱ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላም ለማፅናት ውጤታማ ስራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል። የወልዲያ ከተማ ወጣቶች ጽንፈኛውን አጥብቀው በመታገል ሲያበረክቱት የቆዩትን አስተዋጽኦ ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በውይይቱ የተሳተፉ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስከበር ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በምክክር መድረኩ ላይ ከከተማዋ የተወጣጡ ወጣቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በበጀት አመቱ በከተማዋ በተከናወኑ ስኬታማ የሰላም ተግባራት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ ነበር - የከተማዋ የምክር ቤት አባላት
Jul 11, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት አመቱ በከተማዋ በተከናወኑ ስኬታማ የሰላም ተግባራት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበር የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። 3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ እና የበጀት አመቱ ማጠቃለያ ስብሰባ እየተካሄደ ነው። በስብሰባው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና አቅጣጫዎችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። በዚሁ ጊዜ በ2017 በጀት ዓመት የከተማዋን ሰላም በማስጠበቅ፣ የነዋሪዎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ እንዲሁም አህጉራዊና ዓለም-አቀፋዊ ሁነቶችን በማስተናገድ ስኬታማ ሥራዎች መሰራታቸውን ነው ያብራሩት። በከተማዋ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በርካታ የጸጥታና የወንጀል ድርጊቶችን በመለየትና አስቀድሞ በመከላከል ብሎም ህጋዊ እርምጃዎችን መውሰድ መቻሉን አንስተዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላትም የከተማዋን ሰላምና ደህንነት ከማረጋገጥ አንጻር የተከናወኑት ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊና የምክር ቤቱ አባል ሊዲያ ግርማ በበጀት ዓመቱ በከተማዋ ሰላም በመረጋገጡ የልማት ስራዎች ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲከናወኑ በትኩረት መሰራቱን ገልጸዋል። የከተማው ነዋሪ ህብረተሰብም በወንጀል መከላከል ሂደትና ሰላም በማስጠበቅ ሂደት ላይ የነበረው ተሳትፎ በየጊዜው እየጎለበተ መምጣቱን እንዲሁ። ሰላም ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ልማት የማይተካ ሚና አለው ያሉት ደግሞ ሌላዋ የምክር ቤት አባል ወርቅነሽ ምትኩ (ዶ/ር) ናቸው። በከተማዋ ለተመዘገቡ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጦች የሰላምና ጸጥታ መረጋገጥ ትልቅ ሚና መጫወቱንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ ሌላው የምክር ቤት አባል ኢቲሳ ደሜ(ዶ/ር) ህዝብን ያሳተፈ የሰላምና ልማት ሥራ የተሻለ ውጤት እንደሚያመጣ አዲስ አበባ ማሳያ ናት ብለዋል። ከተማዋ የአህጉራዊና አለም አቀፋዊ ተቋማት መቀመጫና የአፍሪካ መዲና በመሆኗ ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ በኩል ህብረተሰቡ ቀጣይነት ያለው ድጋፉንና ተሳትፎውን ማስቀጠል እንደሚገባ በመጥቀስ። በከተማዋ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንዲረጋገጡ የምክር ቤቱ አባላት ድጋፍና ክትትላቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። የከተማዋን ሰላም በማስቀጠል ሂደትም ነዋሪው ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥል የምክር ቤት አባላቱ ጥሪ አቅርበዋል።
በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ በውጤታማነት ተጠናክሮ ቀጥሏል - ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)
Jul 11, 2025 97
አርባምንጭ ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ) ፡-በሀገሪቱ በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ በውጤታማነት ተጠናክሮ መቀጠሉን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ተናገሩ ። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተገመገመ ነው። የብልጽግና ፓርቲ ዓለም አቀፍና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ በኢኮኖሚው በፖለቲካውና፣ በዲፕሎማሲው ዘርፍ በዓለም አደባባይ ፈጣን ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች ብለዋል። ይህን ለማሳካትም የተረጋጋ የፖለቲካ ምህዳር በመፍጠር በህዝቦች መካከል ወንድማማችነትና እህትማማችነት እየተጠናከረ የመጣበት ዓመት ነው ሲሉም ገልጸዋል። የሀገርን እድገት ወደ ኋላ ለመመለስ የሚጥሩ አካላት በህዝብና በመንግስት ትብብር ሴራቸው እየከሸፈ መምጣቱንም ገልጸዋል። በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ ሂደትም ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ያነሱት ቢቂላ (ዶ/ር) ''እስካሁን የተመዘገበውን ስኬት ለማስቀጠል አበክረን እንሠራለን'' ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው ፓርቲው የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል። የብሔር ብሔረሰቦችን መብት በማስከበር የተረጋጋች ሀገር የመገንባት ሂደቱም በተሻለ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። በቀጣይም የተጀመሩ ልማቶችን በማስቀጠል የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ጠቁመዋል። ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው መድረክ ከሁሉም ክልሎች የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤታማ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገሩ ተግባር ይጠናከራል
Jul 10, 2025 120
ሐረር፤ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)፡-በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤታማ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ በሐረር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲያካሂደው የቆየው የ2017 እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 እቅድ ተግባቦት መድረክ ዛሬ ተጠናቋል። በመድረኩ የፌደራልና የክልል የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ አመራሮች እንዲሁም የፓርቲው የወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ተሳትፈዋል። በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ በ2017 በጀት ዓመት የዴሞክራሲ ባህል እሴትን ለማጠናከር የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር ከመስራት አንጻር በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በጋራ ምክር ቤቶች በመደራጀት አብሮ የመስራት ባህል እየዳበረ መምጣቱን ጠቅሰዋል። ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የተጀመሩ ስራዎች አዲስ ባህልና ልምድ እያመጡ ስለመሆኑም አንስተዋል። የጋራ ስራዎቹ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በቁርጠኝነት መስራታቸውን አጎልብተው እንዲቀጥሉም አመልክተዋል። በአሁኑ ወቅት በየደረጃው ያለው የመንግስት አካላትና ሲቪል ማህበረሰብ በጋራና በቅንጅት የሚሰሩበት ጅምር ሁኔታ መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በተለይ የወጣቶችና ሴቶች አስተዋጽኦን ለማላቅና ተሳትፏቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ብሎም ተጠቃሚነታቸውን ለማጎልበት መድረኩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አንስተዋል። በቀጣይም ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሰረት ትኩረት ተሰጥቶ እና ባህል አድርጎ እንደሚሰራም አመላክተዋል።
የከተማው ነዋሪዎች ሰላምን ለማፅናት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Jul 10, 2025 114
ደብረብርሃን ፤ ሐምሌ 3/ 2017 (ኢዜአ)፡- የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንደገለጹት፤ የጸጥታ ሃይሉ ከሕብረተሰቡ ጋር በመተባበር ሰላም እንዲከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። በዚህም በከተማዋ የሚካሄዱ የኢንዱስትሪ፣ የኢንቨስትመንትና የንግድ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቅሰዋል። ይህም ስራ እድል እንዲስፋፋ፣ የገቢና ሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ እንዲሆኑ ምቹ መደላድል መፍጠሩን ገልጸዋል። በከተማዋ አሁን ላይ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተካሄዱ እንደሚገኙ አስረድተዋል። የልማት ሁሉ መሰረት የሆነውን ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ሁሉ ሕብረተሰቡ ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የተለመደ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላልፈዋል። የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብሩ ዓላማም የከተማው ነዋሪዎች ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የህግ ማስከበር ስራው ይበልጥ በውጤታማነት በማስቀጠሉ ሂደት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ለማበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። ከህግ አስከባሪዎች መካከል ሀምሳ አለቃ ሰይፈ ደምሰው በሰጡት አስተያየት፤ ሰላምን አፅንቶ በማስቀጠል ለልማት የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ይበልጥ ለማጠናከር ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀናጅተወ በትኩረት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ሌላው የመርሃ ግብሩ ተሳታፊ ፈለቀ በየነ በበኩላቸው፤ የአካባቢውን ሰላም በማፅናት የልማት ስራዎቻቸው ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጎዳና ላይ ትርኢቶችና ሌሎች ዝግጅቶች ተካሂደዋል።
ፖለቲካ
የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ብቁ ሰራዊት ከመገንባት በተጓዳኝ ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎችን እየፈጠረ ነው - ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ
Jul 12, 2025 64
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ብቁ ሰራዊት ከመገንባት በተጓዳኝ ዘመኑን የዋጁ ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች እየፈጠረ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጀነራል ከበደ ረጋሳ ገለጹ። ዩኒቨርሲቲው በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ፣ በቢዝነስ፣ በኃብት አስተዳደር እና በሌሎች የትምህርት መርኃ ግብሮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ፤ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ወታደራዊ፣ ሲቪል እና የጎረቤት ሀገራት ተማሪዎችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል ብለዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲው በእውቀትና በክህሎት ብቁ የሆነ የሰው ኃይል እያፈራ መሆኑንም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የመከላከያ ሰራዊቱን የተልዕኮ አፈጻጸም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርሱ ወታደራዊና ሲቪል አመራሮችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ ሀገርን የሚያሻግሩ ሥራዎች በመስራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው የመከላከያን የሰለጠነ የሰራዊት ግንባታ በማገዝ ላይ መሆኑንም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የሰራዊቱን ስምና ዝና በሚመጥን መልኩ የተዋቀረ ሲሆን ከመማር ማስተማር ስራዎች በተጓዳኝ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ስራዎችና ሌሎች ህብረተሰቡን የሚጠቅሙ ተግባራት እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ዘመናዊ ሰራዊት ለመገንባት ከውጭ የምታስገባቸውን ቴክኖሎጂዎች በሀገር ውስጥ ለመተካት ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ስራዎችን በመሥራት ላይ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። ተመራቂዎች ባገኙት እውቀትና ከፍተኛ ክህሎት ሀገራቸውን በብቃት ማገልገል እንደሚገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በ2025 ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 122
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው በተሻሻለው የኢትዮጵያ ምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። አዋጁ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚቀርብ ማንኛውም ቅሬታ በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት የሚደነግግ ሲሆን የምርጫ ክልል አቤቱታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት ከዚህ በፊት ከህብረተሰቡ ይመደብ የነበረው ቀርቶ ቦርዱ አሰልጥኖ በሚመድባቸው የምርጫ አስፈጻሚዎች እንዲተኩ የሚያደርግ ነው። ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ አንድ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመመዝገብ የሚመለምለው አባል ከ5 ክልሎች የነበረ ሲሆን በተሻሻለው አዋጅ አንድ ፓርቲ አባላትን መመልመል ያለበት ከ7 ክልሎች ሊሆን እንደሚገባም በአዋጁ ተመላክቷል። አንድ ፓርቲ ከመንግሥት ድጋፍ ለማግኘት ከ30 በመቶ ከሚሆነው አባሉ የአባልነት መዋጮ መሰብሰብ እንደቅደመ ሁኔታም ተቀምጧል። በአዋጁ መሰረት ጥሰት ፈጽመው የተገኙ ፓርቲዎች እስከ አምስት ዓመት ድረስ ሊታገዱ የሚችሉበት ድንጋጌም ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል ነው። በውይይቱ ከተሳተፉ መካከል የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ በምርጫ ጣቢያ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አይቶ ውሳኔ ይሰጣል የሚለው የአንቀጹ ክፍል ለአተገባበር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል ብለዋል። የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ ባንዲራ በላቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲዎች 30 በመቶ መዋጮ እንዲያሰባስቡ የተቀመጠው ድንጋጌ ከነባራዊ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ወይ የሚለው ሊጤን እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው በአዋጁ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ድንጋጌዎች ሊካተቱ ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሌ በሰጡት ማብራሪያ በአዋጁ ፓርቲዎች 30 በመቶ ያህል መዋጮ ከአባላት ሊሰበሰቡ እንደሚገባ የተደነገገው ፓርቲዎች በመንግሥት በጀት ላይ ብቻ እንዳይመሰረቱና ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። አዋጁ አካል ጉዳተኞችንና ሴቶችን አካታች በሆነና ተሳትፏቸውን በሚያሳድግ መልኩ መቃኘቱን አንስተዋል። የመንግሥት ሰራተኞች በምርጫ ውድድር ወቅት ደሞዛቸውን ይዘው እንዲሳተፉ መደረጉ ለፖለቲካ ምህዳሩ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ነዋይ በሰጡት ማብራሪያ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚነሱ ቅሬታዎች በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ እንዲፈታ አቅጣጫ የተቀመጠው ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታልሞ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲያም ሆኖ ቅሬታዬ አልተፈታም የሚል ማንኛውም አካል ጥያቄውን በየደረጃው የሚያቀርብበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራ አንደሞ በበኩላቸው በህዝባዊ የውይይት መድረኩ የተነሱ ሀሳቦች ለአዋጁ ውሳኔ ሀሳብ የሚረዱ ግበዓቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር ላይ የፓርቲዎች ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በበኩላቸው ፓርቲዎች የወጣቶችን፣ የአካል ጉዳተኞችንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የበለጠ ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአባልነት መዋጮን በተመለከተም ፓርቲዎች አባላቶቻቸውን ሊያበረታቱ እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን ስራ ላይ ለማዋል የጀመራቸውን ተግባራት ሊያጠናክር እንደሚገባ ጠቁመው ፓርቲዎችም ይሄንኑ ስራ ሊደግፉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት ይሰራል - አቶ ፍቃዱ ተሰማ
Jul 11, 2025 81
ጎንደር፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ። ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የተውጣጡ የፓርቲው የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች የተሳተፉበትና በጎንደር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የግምገማ መድረክ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ማምሻውን ተጠናቋል። አቶ ፍቃዱ ተሰማ የግምገማ መድረኩ ማጠቃለያን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ ፓርቲው መጪው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን መላ አባላቱን የማዘጋጀት ስራዎቹን በትኩረት ያከናውናል ብለዋል። ለዚህም የአባላት የስነ-ምግባር ደንቦችን በማዘጋጀት በምርጫው የትብብርና ፉክክር ዴሞክራሲያዊ ባህል እንዲዳብር እንደሚሰራም ተናግረዋል። አባላቱ በፓርቲው እሳቤዎች፣ መተዳደሪያ ደንብና አሰራሮች ዙሪያ ወጥና የተቀራረበ ግንዛቤ በመያዝ ተቋማዊ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ አቅማቸውን የመገንባት ስራ ይከናወናል ብለዋል። የፓርቲው አደረጃጀቶች በልማት በሠላምና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል እንደሚሰሩም ጠቁመዋል። የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደፓርቲና መንግስት ሰፋ ያሉ ውጤቶች የተመዘገቡበትና የማንሰራራት ዘመን በተጨባጭ የታየበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዓመቱ በፓርቲው ውስጥ የአመለካከት፣ የተግባር አንድነትና ህብረ ብሔራዊነት የተጠናከረበት እንደነበርም ተናግረዋል። ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚደረገው ጥረት በጎ ጅምር የታየበት፣ ኢኮኖሚያዊ እድገቱ የሀገሪቱን በጀት በትሪሊዮን እንዲጸድቅ ያስቻለና የእዳ ቅነሳ የተደረገበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራና የከተሞች ኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤታማ እንደነበርም አብራርተዋል፡፡ በሠላም ማስከበር ሂደቱ የታጠቁ ኃይሎች የመንግስትን የሠላም አማራጭ ተቀብለው ተሃድሶ በመውሰድ በስፋት ወደ ሠላማዊ ህይወት መመለሳቸውንም አስታውሰዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳካ ፓርቲው የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ኃላፊው አረጋግጠዋል።
የከተማዋን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ተሳትፏቸውን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል
Jul 11, 2025 44
ወልዲያ ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፡- የወልዲያ ከተማን ሰላም አፅንቶ በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ተሳትፏቸውን ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ገለጹ። የከተማ አስተዳደሩ ከከተማው ወጣቶች ጋር በሰላምና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የምክክር መድረክ ዛሬ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ እንዳሉት፤ የአካባቢን ሠላም ለማፅናት ወጣቱ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የድርሻውን ሲወጣ ቆይቷል። በዚህም የህግ የበላይነትን በማስከበር ሰላም ማስፈን መቻሉን ገልጸው፤ የተገኘውን ሰላም አስጠብቆ ዘላቂ ለማድረግ ወጣቶች ሲያበረክቱ የቆዩትን አስተዋጽኦ ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። በሰሜን ምስራቅ ዕዝ የ801ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ዘውዱ ሰጥአርጌ በበኩላቸው፤ የመከላከያ ሰራዊቱ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላም ለማፅናት ውጤታማ ስራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል። የወልዲያ ከተማ ወጣቶች ጽንፈኛውን አጥብቀው በመታገል ሲያበረክቱት የቆዩትን አስተዋጽኦ ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በውይይቱ የተሳተፉ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስከበር ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በምክክር መድረኩ ላይ ከከተማዋ የተወጣጡ ወጣቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በበጀት አመቱ በከተማዋ በተከናወኑ ስኬታማ የሰላም ተግባራት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ ነበር - የከተማዋ የምክር ቤት አባላት
Jul 11, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት አመቱ በከተማዋ በተከናወኑ ስኬታማ የሰላም ተግባራት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበር የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። 3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ እና የበጀት አመቱ ማጠቃለያ ስብሰባ እየተካሄደ ነው። በስብሰባው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና አቅጣጫዎችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። በዚሁ ጊዜ በ2017 በጀት ዓመት የከተማዋን ሰላም በማስጠበቅ፣ የነዋሪዎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ እንዲሁም አህጉራዊና ዓለም-አቀፋዊ ሁነቶችን በማስተናገድ ስኬታማ ሥራዎች መሰራታቸውን ነው ያብራሩት። በከተማዋ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በርካታ የጸጥታና የወንጀል ድርጊቶችን በመለየትና አስቀድሞ በመከላከል ብሎም ህጋዊ እርምጃዎችን መውሰድ መቻሉን አንስተዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላትም የከተማዋን ሰላምና ደህንነት ከማረጋገጥ አንጻር የተከናወኑት ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊና የምክር ቤቱ አባል ሊዲያ ግርማ በበጀት ዓመቱ በከተማዋ ሰላም በመረጋገጡ የልማት ስራዎች ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲከናወኑ በትኩረት መሰራቱን ገልጸዋል። የከተማው ነዋሪ ህብረተሰብም በወንጀል መከላከል ሂደትና ሰላም በማስጠበቅ ሂደት ላይ የነበረው ተሳትፎ በየጊዜው እየጎለበተ መምጣቱን እንዲሁ። ሰላም ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ልማት የማይተካ ሚና አለው ያሉት ደግሞ ሌላዋ የምክር ቤት አባል ወርቅነሽ ምትኩ (ዶ/ር) ናቸው። በከተማዋ ለተመዘገቡ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጦች የሰላምና ጸጥታ መረጋገጥ ትልቅ ሚና መጫወቱንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ ሌላው የምክር ቤት አባል ኢቲሳ ደሜ(ዶ/ር) ህዝብን ያሳተፈ የሰላምና ልማት ሥራ የተሻለ ውጤት እንደሚያመጣ አዲስ አበባ ማሳያ ናት ብለዋል። ከተማዋ የአህጉራዊና አለም አቀፋዊ ተቋማት መቀመጫና የአፍሪካ መዲና በመሆኗ ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ በኩል ህብረተሰቡ ቀጣይነት ያለው ድጋፉንና ተሳትፎውን ማስቀጠል እንደሚገባ በመጥቀስ። በከተማዋ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንዲረጋገጡ የምክር ቤቱ አባላት ድጋፍና ክትትላቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። የከተማዋን ሰላም በማስቀጠል ሂደትም ነዋሪው ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥል የምክር ቤት አባላቱ ጥሪ አቅርበዋል።
በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ በውጤታማነት ተጠናክሮ ቀጥሏል - ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)
Jul 11, 2025 97
አርባምንጭ ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ) ፡-በሀገሪቱ በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ በውጤታማነት ተጠናክሮ መቀጠሉን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ተናገሩ ። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተገመገመ ነው። የብልጽግና ፓርቲ ዓለም አቀፍና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ በኢኮኖሚው በፖለቲካውና፣ በዲፕሎማሲው ዘርፍ በዓለም አደባባይ ፈጣን ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች ብለዋል። ይህን ለማሳካትም የተረጋጋ የፖለቲካ ምህዳር በመፍጠር በህዝቦች መካከል ወንድማማችነትና እህትማማችነት እየተጠናከረ የመጣበት ዓመት ነው ሲሉም ገልጸዋል። የሀገርን እድገት ወደ ኋላ ለመመለስ የሚጥሩ አካላት በህዝብና በመንግስት ትብብር ሴራቸው እየከሸፈ መምጣቱንም ገልጸዋል። በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ ሂደትም ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ያነሱት ቢቂላ (ዶ/ር) ''እስካሁን የተመዘገበውን ስኬት ለማስቀጠል አበክረን እንሠራለን'' ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው ፓርቲው የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል። የብሔር ብሔረሰቦችን መብት በማስከበር የተረጋጋች ሀገር የመገንባት ሂደቱም በተሻለ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። በቀጣይም የተጀመሩ ልማቶችን በማስቀጠል የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ጠቁመዋል። ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው መድረክ ከሁሉም ክልሎች የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤታማ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገሩ ተግባር ይጠናከራል
Jul 10, 2025 120
ሐረር፤ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)፡-በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤታማ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ በሐረር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲያካሂደው የቆየው የ2017 እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 እቅድ ተግባቦት መድረክ ዛሬ ተጠናቋል። በመድረኩ የፌደራልና የክልል የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ አመራሮች እንዲሁም የፓርቲው የወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ተሳትፈዋል። በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ በ2017 በጀት ዓመት የዴሞክራሲ ባህል እሴትን ለማጠናከር የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር ከመስራት አንጻር በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በጋራ ምክር ቤቶች በመደራጀት አብሮ የመስራት ባህል እየዳበረ መምጣቱን ጠቅሰዋል። ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የተጀመሩ ስራዎች አዲስ ባህልና ልምድ እያመጡ ስለመሆኑም አንስተዋል። የጋራ ስራዎቹ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በቁርጠኝነት መስራታቸውን አጎልብተው እንዲቀጥሉም አመልክተዋል። በአሁኑ ወቅት በየደረጃው ያለው የመንግስት አካላትና ሲቪል ማህበረሰብ በጋራና በቅንጅት የሚሰሩበት ጅምር ሁኔታ መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በተለይ የወጣቶችና ሴቶች አስተዋጽኦን ለማላቅና ተሳትፏቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ብሎም ተጠቃሚነታቸውን ለማጎልበት መድረኩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አንስተዋል። በቀጣይም ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሰረት ትኩረት ተሰጥቶ እና ባህል አድርጎ እንደሚሰራም አመላክተዋል።
የከተማው ነዋሪዎች ሰላምን ለማፅናት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Jul 10, 2025 114
ደብረብርሃን ፤ ሐምሌ 3/ 2017 (ኢዜአ)፡- የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንደገለጹት፤ የጸጥታ ሃይሉ ከሕብረተሰቡ ጋር በመተባበር ሰላም እንዲከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። በዚህም በከተማዋ የሚካሄዱ የኢንዱስትሪ፣ የኢንቨስትመንትና የንግድ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቅሰዋል። ይህም ስራ እድል እንዲስፋፋ፣ የገቢና ሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ እንዲሆኑ ምቹ መደላድል መፍጠሩን ገልጸዋል። በከተማዋ አሁን ላይ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተካሄዱ እንደሚገኙ አስረድተዋል። የልማት ሁሉ መሰረት የሆነውን ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ሁሉ ሕብረተሰቡ ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የተለመደ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላልፈዋል። የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብሩ ዓላማም የከተማው ነዋሪዎች ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የህግ ማስከበር ስራው ይበልጥ በውጤታማነት በማስቀጠሉ ሂደት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ለማበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። ከህግ አስከባሪዎች መካከል ሀምሳ አለቃ ሰይፈ ደምሰው በሰጡት አስተያየት፤ ሰላምን አፅንቶ በማስቀጠል ለልማት የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ይበልጥ ለማጠናከር ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀናጅተወ በትኩረት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ሌላው የመርሃ ግብሩ ተሳታፊ ፈለቀ በየነ በበኩላቸው፤ የአካባቢውን ሰላም በማፅናት የልማት ስራዎቻቸው ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጎዳና ላይ ትርኢቶችና ሌሎች ዝግጅቶች ተካሂደዋል።
ማህበራዊ
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መደጋገፍንና አብሮነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ ይከናወናል
Jul 12, 2025 20
አበሽጌ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፡- የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መደጋገፍንና አብሮነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከናወን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሀላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አለምፀሐይ ጳውሎስ ገለጹ። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እና ተጠሪ ተቋማት በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብርን ዛሬ አስጀምረዋል። በዚህ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሀላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አለምፀሐይ ጳውሎስ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መደጋገፍንና አብሮነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ ይከናወናል ብለዋል። በወረዳው ከ33 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተለያዩ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት እንደሚከናወኑም ተናግረዋል። ከሚከናወኑት ተግባራት መካከል 15 የአቅመ ደካማ ወገኖች መኖሪያ ቤቶችና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ እንዲሁም የችግረኛ ቤተሰብ አባላት ለሆኑ ለ2ሺህ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶች ድጋፍ እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል። በተጨማሪም የኮሪደር መንደር እንደሚገነባ ያመለከቱት ሀላፊ ሚኒስትሯ አትክልት እና ፍራፍሬ ልማትን ጨምሮ ሕብረተሰቡን በተለይም ወጣቱን በማሳተፍ የማስፋፋት ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል። በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ በተጀመረው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እና ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የጉራጌ ዞን ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በክረምት ህክምና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለአምስት ሚሊዮን ዜጎች ነፃ የጤና አገልግሎት ይሰጣል - ዶክተር መቅደስ ዳባ
Jul 12, 2025 32
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ2017ዓ.ም የክረምት ህክምና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለአምስት ሚሊዮን ዜጎች ነፃ የጤና አገልግሎት እንደሚሰጥ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ አስታወቁ። እስካሁን በተከናወነው የክረምት ህክምና በጎ ፈቃድ አገልግሎት 10 ሚሊዮን ዜጎች የነፃ የጤና አገልግሎት ማግኘታቸውን አመልክተው፤ 12 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውንም ተናግረዋል። ሀገር አቀፍ ነፃ የክረምት የጤና ምርመራ፣ የምክርና የሕክምና አገልግሎት መርሃ ግብር በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዛሬ ተጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የተጠሪ ተቋማትና የጤና ተቋማት አመራር አባላትን ጨምሮ የተለያዩ እንግዶች ተገኝተዋል። ዶክተር መቅደስ ዳባ በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለፁት፤ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የምርመራና ህክምና ነጻ አገልግሎት ከመስጠት ባሻገር የደም ልገሳ፣ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ዜጎች የቤት እድሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍና የችግኝ ተከላ ይከናወናል። በክረምቱ ወቅት ለአምስት ሚሊዮን ዜጎች ነፃ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት የታቀደ መሆኑን ጠቁመው፤ 250ሺህ ችግኞችን መትከል፣ 17 ጤና ተቋማት እድሳት፣ 40 የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታና ለስድስት ሺህ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚደረግም ተናግረዋል። ፅዱ የጤና ተቋማት መፍጠር የሚያስችል የፅዳት ዘመቻ፣ የወባ መከላከል ስራና ሌሎች ተግባራት እንደሚከናወኑም ነው የገለጹት። ከ2011ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2016 ዓ.ም በተከናወነው የክረምት የህክምና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለ10 ሚሊዮን ዜጎች ነፃ የህክምና አገልግሎት መሰጠቱንና ከ400ሺህ ዩኒት በላይ ደም መሰብሰቡን ተናግረዋል። አምና በተደረገው የክረምት ህክምና በጎ ፈቃድ ከ400 በላይ የተበላሹ የህክምና መሳሪያዎችን በመጠገን ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ወጪ ማዳን መቻሉን ጠቁመዋል። የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዳይሬክተር ዶክተር ሽመልስ ገዛኸኝ እንዳሉት፤ በ2016 በክረምት በጎ ፈቃድ ሆስፒታሉ ነፃ የጤና ምርመራ፣ የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳት፣ ደም ልገሳና ሌሎች ተግባራትን አከናውኗል። በክረምት በጎ ፈቃድ የተጀመረው መርሃ-ግብር በበጋም ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ ለ2016 ዓ.ም በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊዎች የዕውቅና መርሀ ግብር ተካሂዷል።
በሐረሪ ክልል ከ40ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች የሚሳተፉበት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ይከናወናል - ቢሮው
Jul 12, 2025 39
ሐረር፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ከ40ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች የሚሳተፉበት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እንደሚከናወን የክልሉ ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደውን ክልላዊ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል። በክልሉ የገጠር እና ከተማ ወረዳዎች በአቅመ ደካማ ቤት እድሳትና ችግኝ ተከላ ሥራ በተጀመረው መርሃ ግብር ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር፣ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ጌቱ ወየሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ አመራሮች ተገኝተዋል። የክልሉ ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ረምዝያ አብዱልዋህብ በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ በክልሉ በየዓመቱ በሚከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተሳታፊ ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። በተያዘው የክርምት ወራትም በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራትን ለማከናወን እቅድ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን ነው የተናገሩት። በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራው ከ40ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች እንደሚሳተፉ ጠቁመው በአገልግሎቱም 14 የትኩረት መስኮች ተለይተው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያድርጉ የልማት ሥራዎች እንደሚከናወኑ ገልጸዋል። በክልሉ ባለፈው ዓመት በበጎፈቃድ አገልግሎት ከ190 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውንም ወይዘሮ ረምዝያ አመልክተዋል።
በከተማዋ ተገንብተው የተመረቁ መሰረተ ልማቶች አገልግሎቶችን በቅርበት እንድናገኝ ያስችሉናል - ነዋሪዎች
Jul 12, 2025 32
አዳማ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በአዳማ ከተማ ተገንብተው የተመረቁ መሰረተ ልማቶች አገልግሎቶችን በቅርበት ማግኘት እንደሚያስችላቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። የኦሮሚያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ግንባታቸው የተጠናቀቁ መሰረተ ልማቶችን ለአገልግሎት ክፍት ሲያደርግ መቆይቱ ይታወቃል። የአዳማ ከተማ አስተዳደርም የከተማዋን ነዋሪዎች ሁሉን አቀፍ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሰረተ ልማቶችን ለአገልግሎት አብቅቷል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ሰሞኑን ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት መሰረተ ልማቶች ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እንቅስቃሴያቸውን በማፋጠን ኑሯቸውን ለመለወጥ የሚያግዟቸው እንደሆኑ ተናግረዋል። ከአዳማ ከተማ የቦሌ ክፍለ ከተማ ጎሮ ወረዳ ነዋሪ ሸሪፍ ኢብራሂም እንደገለፁት ቀደም ባለው ጊዜ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በአካባቢያቸው ባለመኖሩ እድሜያቸው ለቅድመ መደበኛ ትምህርት የደረሱ ሕጻናት የትምህርት እድል በቅርበት አያገኙም ነበር። ከአካባቢያቸው ራቅ ብሎ በሚገኝ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ወስዶ ለማስተማርም ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ያለበት መንገድ ማቋረጥ ግድ ስለሆነ ለደህንነታቸው ስለምንሰጋ ቤት እናውላቸው ነበር ብለዋል። በአሁኑ ወቅት 'ቡኡራ ቦሩ' የተሰኘ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በአካባቢያቸው መገንባቱ ህጻናት ልጆች የቅድመ መደበኛ ትምህርት ተጠቃሚ መሆን እንዳስቻላቸው ገልጸዋል። የትምህርት ቤቱ መገንባት የትራንስፖርት ወጪና እንግልትን ያስቀረ ከመሆኑም ባለፈ በቅርበት ትምህርት ቤት በማግኘታቸው ለልጆቻቸው የወደ ፊት እጣ ፈንታም መልካም ሁኔታ የፈጠረ ነው ብለዋል። በከተማ አስተዳደሩ የተገነቡ የመዝናኛ ማዕከላት በስራ የደከመ አዕምሯችንን ለማዝናናት ምቹ ሁኔታ ፈጥረዋል ያለው ደግሞ የደንበላ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ወጣት እዮብ ክንዴ ነው። የመዝናኛ ስፍራዎች በተለይ የከተማው ወጣቶች አልባሌ ቦታ ከመዋል ይልቅ ጊዜያቸውን በጥሩ እና ያማረ ስፍራ እንዲያሳልፉ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። ሌላው የዚሁ ወረዳ ነዋሪ አቶ ለሚ ባለሚ በበኩላቸው አሁን በአካባቢያችን ያማረ መዝናኛ ስፍራ የተሰራበት ቦታ ቆሻሻ የሚጣልበትና ለእይታም የማይማርክ ነበር ይላሉ። ስፍራው የከተማዋ ወጣቶችና አዛውንቶች ጭምር የሚዝናኑበት፣ እረፍት የሚያደረጉበትና የተለያዩ አገልግሎቶች የሚያገኙበት ሆኗል ብለዋል። በደንበላ ክፍለ ከተማ የወንጂ የወተት ላሞችና የሥጋ ከብቶች ማድለቢያ ማዕከል ውስጥ የመስሪያ ቦታ ተጠቃሚ የሆኑት አርሶ አደር ተስፋዬ ካሳ፣ ከዚህ በፊት የእንስሳት ማድለብ ስራችንን የምናከናውነው በመኖሪያ ቤት ውስጥ ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በከተማ አስተዳደሩ የወተት ላሞችና ለስጋ የሚሆኑ በሬዎች የሚያደልቡበት ዘመናዊ ማዕከል በማግኘታቸው መንግስትን አመስግነዋል። የተሻለ የወተት ምርት የሚሰጡ ላሞችን ወደ ማዕከሉ በማስገባት በዘመናዊ መልኩ ለማርባት አቅደን ወደ ስራ ገብተናል ብለዋል። ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት ለአገልግሎት ክፍት የሆኑ መሰረተ ልማቶች መሰረታዊ አገልግሎት በቅርበት ማግኘት የሚያስችሏቸው ናቸው።
ኢኮኖሚ
የመዲናዋ የ2018 በጀት 350 ነጥብ 13 ቢሊዮን ብር ሆኖ ጸደቀ
Jul 12, 2025 29
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የመዲናዋን የ2018 በጀት 350 ነጥብ 13 ቢሊዮን ብር አድርጎ አጸደቀ፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂዷል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ አብዱልቃድር ሬድዋን፥ የከተማ አስተዳደሩን የ2018 በጀት ዓመት ዝርዝር ረቂቅ በጀት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። ለ2018 በጀት ዓመት 350 ነጥብ 13 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን ገልጸው፥ በጀቱ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ108 ቢሊየን ብር ወይም የ45 በመቶ እድገት እንዳለው ገልጸዋል። ከአጠቃላዩ በጀት ለመደበኛ ወጪ 91 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር፣ ለካፒታል ሥራዎች 246 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲሆን ቀሪው 12 ቢሊዮን ብር ለመጠባበቂያ መሆኑን አብራርተዋል። የካፒታል በጀት ከፍ እንዲል የተደረገው ለሰው ተኮር ሥራዎች፣ ለቤት ልማት፣ ለኮሪደር ልማት እና ለከተማ አስተዳደሩ ወሳኝ ፕሮጀክቶች ትኩረት መስጠት በማስፈለጉ መሆኑን አንስተዋል። በጀቱ የከተማዋን ራዕይ፣ በሒደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችንና አዳዲስ የልማት ፍላጎቶችን፣ የታቀዱ አስተዳደራዊ ማሻሻያዎችን፣ አገልግሎት የማዘመን ስራን በፍጥነትና በውጤታማነት ለመተግበር ታሳቢ በማድረግ መዘጋጀቱን አስረድተዋል፡፡ ከአጠቃላይ በጀቱ ከ238 ቢሊየን ብር በላይ የሚሆነው ከታክስ፣ ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ከ56 ቢሊየን ብር በላይ፣ ታክስ ካልሆነ ገቢ ከ46 ቢሊየን ብር በላይ፣ ከመንገድ ፈንድ 1.8 ቢሊየን፣ ከውጭ ብድርና እርዳታ 6 ነጥብ 98 ቢሊየን ብር እንደሚሰበሰብ ጠቅሰዋል። የምክር ቤቱ አባላትም በረቂቅ በጀቱ ላይ በመወያየት በሙሉ ድምጽ አጽድቀውታል።
በከተማዋ የህዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጠንካራ ቁጥጥርና ክትትልተደርጓል
Jul 12, 2025 34
አዳማ፤ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጠንካራ ቁጥጥርና ክትትል መደረጉን የከተማዋ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ገለጹ። የከተማዋ ምክር ቤት 12ኛ ዓመት ሁለተኛ የስራ ዘመን 48ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። የአዳማ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ እመቤት ጂባ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህዝቡ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ምክር ቤቱ የሚጠበቅበትን ሲወጣ ቆይቷል። በተለይም የህዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጠንካራ ቁጥጥርና ክትትል መደረጉን ተናግረዋል። በዚህም የልማት ፕሮጀክቶች በወቅቱ እንዲጠናቀቁ፣ የስማርት አዳማ ፕሮጀክት ውጤታማነትና የአገልግሎት አሰጣጥ ዲጂታል እንዲሆን በማስቻል ረገድ ምክር ቤቱ ሚናውን በአግባቡ ሲወጣ መቆየቱን ገልጸዋል። ይህም በመሆኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል የቻሉ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን አውስተዋል። በከተማዋ የተጀመሩ አገልግሎትን የማዘመንና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ በቀጣይም የምክር ቤት አባላቱ ድጋፍ፣ ክትትልና ቁጥጥር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ለምክር ቤቱ የበጀት ዓመቱን እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ፤ በበጀት ዓመቱ የከተማዋን ነዋሪዎች ፍላጎት ያማከሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በከተማ አስተዳደሩ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታና አገልግሎትን በማዘመን ረገድ የተሻለ ስራ መከናወኑን ጠቅሰው የጎጆ ኢንዱስትሪን ጨምሮ ከ51 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች የስራ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ሲሆን በሰብል ልማት፣ በእንስሳት ዝሪያ ማሻሻል፣ በዶሮ፣ በዓሣና በከብት ማድለብ አበረታች ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል። በከተማው ከ3 ሺህ 500 በላይ ሼዶች ተገንብተው ለወጣቶች፣ ማህበራትና አርሶ አደሮች መተላለፋቸውን ጠቅሰው ይህም የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ለማሳካት እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል። ከዚህም ባለፈ በአካባቢ ጥበቃ፣ በጽዳት፣ በውበትና አረንጓዴነት ላይ በተሰራው ስራ ከተማዋ የተሻለ ገጽታ እየተላበሰች መሆኗን ተናግረዋል። የከተማዋን ገቢ ለማሳደግ በተሰራው ስራ በበጀት ዓመቱ ከ12 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉንም አመልክተዋል። በበጀት ዓመቱ ድህነትን ለመቀነስ ወሳኝ ሚና ያላቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ በተሰራው ስራ 171 ፕሮጀክቶች ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል ብለዋል። የመሬት ሀብትን በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል በተሰራው ስራ የካዳስተር ምዝገባን በማጠናቀቅ ዘመናዊ የመሬት አስተዳድር ስርዓት እውን ማድረግ መቻሉንም ገልጸዋል።
ከጋምቤላ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ5 ሺህ 429 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል
Jul 12, 2025 42
ጋምቤላ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ ከጋምቤላ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ5 ሺህ 429 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን የክልሉ ማዕድን ኃብት ልማት አስታወቀ። በክልሉ በበጀት ዓመቱ ገቢ የተደረገው የወርቅ ምርት መጠን ከእቅዱ አንጻር የ2ሺህ 578 ኪሎ ግራም ብልጫ እንዳለውም ተመልክቷል። አንደ ሀገር የታለመውን የእድገትና የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ከተለዩት አምስት የብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል አንዱ የወርቅ ማዕድን ነው። በዘርፉ የታለመውን ግብ ለማሳካት የተቀየሱ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ መግለፃቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሳያነትም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለውጪ ገበያ የቀረበው ወርቅ ወደ 37 ቶን ከፍ ማለቱን ለምክር ቤቱ ማብራሪያ መስጠታቸው የሚታወስ ነው። የጋምቤላ ክልል የማዕድን ኃብት ልማት ዋና ዳይሬክተር ኡጁሉ ጊሎ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት በክልሉ የወርቅ ማዕድን ልማት ግብ ለማሳካት በተከናወኑት ተግባራት ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል። በክልሉ በበጀት ዓመቱ 2ሺህ 850 ኪሎ ግራም የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ለማድረግ ታቅዶ ከ5ሺህ 429 ኪሎ ግራም በላይ ገቢ መደረጉን በማሳያነት ጠቅሰዋል። በበጀት ዓመቱ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ የተደረገው የወርቅ ማዕድን ከእቅዱ በ2 ሺህ 578 ኪሎ ግራም ብልጫ ያለው መሆኑን ጠቁመው ይህም ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ5ሺህ 119 ኪሎ ግራም እንደሚበልጥ ገልጸዋል። በክልሉ በበጀት ዓመቱ ወደ ብሔራዊ ባንክ የገባው የወርቅ ምርት በዲማ፣ በጋምቤላ፣ በአቦቦና በመንጊሽ ወረዳዎች በባህላዊ፣ በልዩ አነስተኛና በትላልቅ የወርቅ አምራች ኩባንያዎች የተመረተ ነው ብለዋል። በዘርፉ የስራ እድልን ለመፍጠር በተደረገው ጥረትም ከ7ሺህ 680 በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። በክልሉ በበጀት ዓመቱ የተሻለ የወርቅ ምርትና ግብይት ሊከናወን የቻለው ከክልል እስከ ወረዳ በተከናወነው የክትትልና ድጋፍ እንዲሁም በክልሉ በተፈጠረው ሰላም በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ በመግባታቸው ነው ብለዋል።
የበደሌ ከተማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብና ጽዱ ያደረጋት በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት
Jul 12, 2025 40
በደሌ፣ሀምሌ 5/2017(ኢዜአ)፡- የበደሌ ከተማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብና ጽዱ ያደረጋት በመሆኑ ስራው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ ነዋሪዎች ተናገሩ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ነዋሪዎች እንደሚሉት የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን የተሻለ ገጽታ እና ውበት ከማላበስ ባለፈ መንገድ በማስፋቱ ለእንቅስቃሴ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ከነዋሪዎቹ መካከል ወጣት ጌታሁን ተፈሪ፤ የኮሪደር ልማት ከመገንባቱ በፊት መንገዶች ጠባብ እና የተጨናነቁ በመሆናቸው ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ እንደነበር ተናግሯል። የኮሪደር ልማቱ ከተገነባ ወዲህ ሱቆችና ንግድ ቤቶች ጭምር ለስራ ምቹ ከመሆናቸው አልፎ ገጽታቸውም ተቀይሯል ብሏል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ኢሳያስ ጌታሁን በከተማዋ በመንገዶች ጥበት ምክኒያት ለትራፊክ አደጋ አጋላጭ ሁኔታዎች እንደነበሩ ተናግረዋል። በተለይም የተሽከርካሪና የአግረኛ መንገድ መለየቱ አደጋን ከመቀነስ አልፎ መንገድ ላይ በእግር ለመራመድ የተመቸ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። የከተማው የኮሪደር ልማት ስራ የበለጠ እንዲሰፋ እና ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያመለከቱት ነዋሪው በስራው የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የከተማው የኮሪደር ልማት ለእግረኛ ምቹ ሁነታ የፈጠረ፤ ከተማዋን ማራኪ ገጽታ ያላበሰ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ ዳንኤል ካሳሁን ናቸው። ''የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ የስራ እድል የፈጠረ እንዲሁም የከተማችንን ገጽታ የቀየረ ልማት በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት'' ብለዋል። የበደሌ ከተማ ከንቲባ አቶ ጸጋዬ ተሾመ፤ የኮሪደር ልማቱ በትኩረት ሲከናወን መቆየቱን እና በስራውም ትልቅ ለውጥ መታየቱን አስረድተዋል። በከተማው በጅማ፣ በወለጋ እና በጎሬ መውጫ በሮች ተለይተው የኮሪደር ልማት ስራው ሲከናወን መቆየቱን ገልጸው የኮሪደር ልማት ስራውም የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ይገኛል ብለዋል። እስካሁን ድረስ የተሰራው የኮሪደር ልማት ስምንት ኪሎሜትር የሚሸፍን መሆኑን ጠቅሰው ከ5 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩንም አውስተዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ዩኒቨርሲቲው ዘመናዊ የሠራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ የሚያጠናክሩ ብቁ ሙያተኞች እያፈራ ነው - ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር)
Jul 12, 2025 20
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ የሚያጠናክሩ ብቃትና ሥነ-ምግባር ያላቸው ሙያተኞች እያፈራ እንደሚገኝ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ፣ በቢዝነስ እና በኃብት አስተዳደር እንዲሁም በሌሎች የትምህርት መርኃ ግብሮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የዛሬው ተመራቂዎች ኢትዮጵያ በየዘመኑ ጀግኖችን የምታፈራ ሀገር ለመሆኗ ትልቅ ማሣያ ናችሁ ብለዋል። የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ የሰለጠነ የሠራዊት አባላትንና ሲቪል አመራር በማፍራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው በዚህም በእውቀት፣ በዓላማና በሙያዊ ልህቀት የታነጹ ሙያተኞችን እያፈራ ይገኛል ብለዋል። የሠራዊቱን የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ብቃት ለማላቅ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይም ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ ማገዝ የሚችሉ ብቁና ሥነ-ምግባር ያላቸውን ሙያተኞች እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል። በሌላ መልኩም በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም ሚኒስትሯ ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው ለሀገርና ለመጪው ትውልድ የሚሻገር ስራ መሥራቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል። ተመራቂዎች በታማኝነት፣ በቅንነትና በስነምግባር ሀገራቸውን ማገልገል እንዳለባቸው በአፅንኦት ተናግረዋል። በምርቃት መርኃ ግብሩ ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ሽልማት ተበርክቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በ2025 ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
የኢትዮጵያ ታዳጊዎችና ወጣቶች በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቷል - ኢንስቲትዩቱ
Jul 12, 2025 47
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታዳጊዎችና ወጣቶች በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ገለፁ። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በተለያዩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች 4ኛውን የታዳጊዎች የክረምት ስልጠና በሳይንስ ሙዚየም አስጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ሰልጣኞችና የሰልጣኞች ወላጆች ተገኝተዋል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ታዳጊዎችንና ወጣቶችን ለማብቃት በክረምት ስልጠና እንዲሁም ከትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር እውቀትና ችሎታ እንዲያዳብሩ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሀገራት ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት ቁልፍ መሳሪያ እየሆነ መምጣቱን አንስተዋል። ኢትዮጵያም በሁሉም መስክ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ለመጠቀም ሀገር ተረካቢ የሆኑ ታዳጊዎችና ወጣቶች በዘርፉ እውቀትና ክህሎት እንዲኖራቸው ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኗን ተናግረዋል። በዘርፉ መሰረታዊ እውቀት ኖሯቸው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። በ4ኛው ዙር የክረምት ስልጠና ለመውሰድ ከተመዘገቡ 3ሺህ ታዳጊዎች መካከል 300ዎቹ መስፈርቱን አሟልተው ወደ ስልጠና መግባታቸው ተገልጿል። ስልጠናው ለሁለት ወራት የሚሰጥ ሲሆን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሰረታውያን፣ ሮቦቲክስ፣ ፕሮግራሚንግና ሌሎች ትምህርቶችን ይወስዳሉ ተብሏል።
የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች ለሀገር እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መደላድል ይፈጥራል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 106
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ያላቸውን ሚና በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መደላድል እንደሚፈጥር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። ቋሚ ኮሚቴው የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት የባለድርሻ አካላት አስረጂ መድረክ አካሂዷል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ቤተልሔም ላቀው(ዶ/ር) ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ በቋሚ ኮሜቴው የተዘጋጁ ጥያቄዎችን በዝርዝር አቅርበዋል። በረቂቅ አዋጁ የተካተቱ አንቀጾች ላይ የሚስተዋሉ የግልጽነትና የትርጓሜ ለውጥ የሚያመጡ ሃሳቦች በድጋሚ ሊፈተሹ እንደሚገባ አንስተዋል። እንዲሁም የረቂቅ አዋጁን የህግ ማዕቀፍ ዝግጅት፣ የአጋር አካላት ሚና እና የአዋጁን አስፈላጊነት በሚመለከት ማብራሪያ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር)፤ ከቋሚ ኮሚቴው ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በምላሻቸውም ረቂቅ አዋጁ እንደሀገር የሃብት ምንጭ የሆኑ አዳዲስ አማራጮችንና አሰራሮችን ለማስፋት ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል። በዋናነት መንግስት የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለውን ተግባር ''ከሃሳብ እስከ አምራችነት'' የሚለውን እሳቤ የሚደግፍ መሆኑንም አንስተዋል። ረቂቅ አዋጁ የወጣቱን አምራችነት ለማሳደግ እንዲያግዝ ታልሞ በጥንቃቄ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመው፥ ለዚህም አስቻይ የሆኑ የህግ ማዕቀፎችን ለማካተት ጥረት ተደርጓል ነው ያሉት። ቋሚ ኮሚቴው ረቂቅ አዋጁን በሚመለከት የሰጠው ግብረ መልስ ጉድለቶችን ለማረምና ለመፈተሽ የሚያግዝ በመሆኑ የቀጣይ የቤት ስራ በማድረግ የመፈተሽ ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ረቂቅ አዋጁ ሀገሪቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላትን የማምረት አቅም ለማጉላት እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በተጨማሪም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያለው አበርክቶ የጎላ መሆኑን ገልጸው፤ በእውቀትና ፈጠራ የተመሰረተ ኢኮኖሚ ለመገንባት አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቁመዋል። ረቂቅ አዋጁን ይበልጥ ለማዳበር ስታርታፖችንና ባለድርሻ አካላትን በቅርበት የማወያየትና ግብዓት የማሰባሰብ ስራ መከናወኑን ጠቁመዋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በሰጡት ማጠቃለያ፤ የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ለአካታች ኢኮኖሚ ግንባታ አስቻይ ሁኔታን እንደሚፈጥር አብራርተዋል። ረቂቅ አዋጁ ኢትዮጵያ ያላትን የወጣት ኃይል በተገቢው መልኩ ለመጠቀምና የፈጠራ ሃሳብ ጥቅም ላይ እንዲውል ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። የተለያየ የፈጠራ ሃሳብ፣ ችሎታና በቴክኖሎጂ የዳበረ እውቀት ያላቸው ስታርታፖች በመረጡት መስክ ተሰማርተው ከሀገር አልፎ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አዋጁ አዎንታዊ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል። የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ያላቸውን ሚና በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑንም ገልጸዋል።
በዞኑ በዲጂታላይዜሽን የታገዘ አገልግሎት ለማህበረሰቡ በመስጠት የተገልጋይን እርካታ ለማረጋገጥ ትኩረት ተደርጓል
Jul 10, 2025 106
ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦በሰሜን ሸዋ ዞን በዲጂታላይዜሽን የታገዘ ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት ለማህበረሰቡ በመስጠት የተገልጋይን እርካታ ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። የሰሜን ሸዋ ዞን የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ በከተሞች የኮሪደር ልማትና በዲጂታላይዜሽን አተገባበር ላይ ዛሬ ከባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በውይይቱ ላይ እንደገለጹት በከተሞች ተአማኒነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ዲጂታላይዜሽን የአሰራር ሥርአት እየተዘረጋ ነው። የዲጂታል አሰራሩ በየደረጃው ያሉ የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች ለተገልጋዩ ማህበረሰብ ግልጽና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ ባለፈ ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ያግዛል ብለዋል። በአዲሱ በጀት ዓመት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የተገልጋይን እርካታ ለመፍጠር ከሚሰራው ሥራ በተጨማሪ በከተሞችና በገጠር አካባቢዎች የኮሪደር ልማትን በማስጀመር የህብረተሰቡን አኗኗር ለማዘመን ትኩረት እንደሚሰጥም አስገንዝበዋል። የዞኑ ከተሞችና የገጠር አካባቢዎች ለማዘመን በሚሰራው ሥራም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አስተዳዳሪው አሳስበዋል። በዞኑ የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ብርቃብርቅ ተሾመ በበኩላቸው እንዳሉት ከተሞችን ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ ነው። ለዚህም በዞኑ ሥር ባለችው የሸዋ ሮቢት ከተማ የኮሪደር ልማት ግንባታ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ተጀምሮ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ቡልጋ፣ አረርቲና ለሚ ከተሞችን ጨምሮ በዞኑ ሥር ባሉ ዘጠኝ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራን ለማስጀመር የሚያስችል የጥናት ሥራ ተጠናቋል ብለዋል። የአረርቲ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ መሳይ አስታጥቄ በከተማው የኮሪደር ልማት ሥራን ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል። ልማቱንና የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማስመልከት ከከተማዋ ነዋሪዎች ጋር በስፋት ውይይት ተደርጎ የጋራ መግባባት ላይ መደረሱንም ጠቁመዋል። የእንሳሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አከበረኝ ዓለሙ በበኩላቸው እንደገለጹት ከሀገራዊ ለውጡ በፊት ተረስተው የቆዩ ከተሞች አሁን ላይ ትኩረት እያገኙ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለዚህም የለሚ ከተማ በኢንቨስትመንት እያደገች መምጣቷ አንዱ ማሳያ ነው ያሉት አቶ አከበረኝ፣ በአዲሱ በጀት ዓመት በከተማው የኮሪደር ልማትና የዲጂታላይዜሽን አሰራርን ለመጀመር ዝግጅት መደረጉን ጠቅስዋል። በውይይቱ ላይ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ስፖርት
የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ
Jul 12, 2025 14
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ ሶስተኛ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ። ከምሽቱ 4 ላይ አዘጋጇ ሞሮኮ ከሴኔጋል በፕሪስን ሙላይ አብደላ ስታዲየም ይጫወታሉ። በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ዛምቢያ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኤል ባቺር ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ሞሮኮ አራት ነጥብ በመያዝ ምድቡን በአራት ነጥብ እየመራች ትገኛለች። ሴኔጋል በሶስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛለች። አዘጋጅ ሀገር ሞሮኮ ማሸነፍ ወይም አቻ መውጣት ወደ ሩብ ፍጻሜው ያሳልፋታል። ተሸንፋም ጥሩ ሶስተኛ ሆኖ የማለፍ እድል አላት። ሴኔጋል ካሸነፈች በቀጥታ ሩብ ፍጻሜውን ትቀላቀላለች። አቻ መውጣት ወይም መሸነፍ ሁለተኛ አሊያም ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ እንድታልፍ ሊያደርጋት ይችላል። ዛምቢያ በምድቡ አራት ነጥብ በመሰብሰብ ተመሳሳይ ነጥብ ባላት አዘጋጇ ሞሮኮ በግብ ክፍያ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። ማሸነፍ ዛምቢያ የማንንም ውጤት ሳትጠብቅ ወደ ሩብ ፍጻሜ እንድትገባ ያስችላታል። ተሸንፋ ወይም አቻ ወጥታ በሂሳባዊ ስሌት ቀጣዩን ዙር የመቀላቀል እድል ልታገኝ ትችላለች። ሁለት ሽንፈት ያስተናገደችው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛለች። ማሸነፍ የኮንጎን ምርጥ ሶስተኛ ሆና የማለፍ እድሏን ሊያለመልመው ይችላል።
ታንዛንያ እና ደቡብ አፍሪካ ነጥብ ተጋርተዋል
Jul 12, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት መርሃ ግብር ታንዛንያ እና ደቡብ አፍሪካ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ትናንት ማምሻውን በሆነር ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አጥቂዋ ኦፓ ክሌመንት በ24ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠረችው ግብ ታንዛንያ መሪ ሆናለች። የተከላካይ መስመር ተሰላፊዋ ባምባናኒ ምባኔ በ70ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ላይ ያሳረፈችው ጎል ደቡብ አፍሪካን አቻ አድርጓል። የታንዛንያዋ ኤልሳቤት ጆን ቼንጌ በ84ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ሜዳ ተሰናብታለች። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ደቡብ አፍሪካ በአራት ነጥብ የምድቡን መሪነት ከማሊ ተረክባለች። ታንዛንያ በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዚሁ ምድብ ትናንት በተደረገ ጨዋታ ጋና እና ማሊ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ደቡብ አፍሪካ ከማሊ፣ ጋና ከታንዛንያ የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም የመጨረሻ የምድብ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ጋና እና ማሊ ነጥብ ተጋሩ
Jul 11, 2025 80
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት ጨዋታ ጋና እና ማሊ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ማምሻውን በቤርካኔ ሙኒሲፓል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የአማካይ መስመር ተሰላፊዋ አሊስ ኩሲ በስድስተኛው ደቂቃ ያስቆጠረችው ግብ ጋናን መሪ መሆን ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ አጥቂዋ አይሳታ ትራኦሬ በ52ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፈችው ግብ ማሊን አቻ አድርጋለች። በጨዋታው ብልጫ ወስዳ የተጫወተችው ጋና ያገኘቻቸውን ግልጽ የግብ እድሎች አልተጠቀመችበትም። ውጤቱን ተከትሎ ማሊ ነጥቧን ወደ አራት ከፍ በማድረግ በምድብ መሪነቷ ቀጥላለች። ጋና በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ዙር የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ
Jul 11, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የሰባተኛ ቀን ውሎ የምድብ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምዕራብ አፍሪካውያኑ ጋና እና ማሊ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ በቤርካኔ ሙኒሲፓል ስታዲየም ይጫወታሉ። ጋና በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በደቡብ አፍሪካ የ2 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። ማሊ በበኩሏ ታንዛንያን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ጋና በውድድሩ ለመቆየት የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ ይኖርባታል። በአንጻሩ ማሊ ድል ከቀናት ሩብ ፍጻሜውን ትቀላቀላለች። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም አምስት ጊዜ እርስ በእርስ ተጫውተው ጋና ሶስት ጊዜ ስታሸንፍ ማሊ አንድ ጊዜ ድል ቀንቷታል። በቀሪው ጨዋታ ነጥብ ተጋርተዋል። በጨዋታዎቹ ጋና 15 ግቦችን ከመረብ ጋር ስታገናኝ ማሊ 12 ግቦችን አስቆጥራለች። ባላቸው የእርስ በእርስ ታሪክ ጋና የተሻለ የማሸነፍ ግምት ብታገኝም በጥሩ ወቅታዊ ብቃት ላይ የምትገኘው ማሊ ተጋጣሚዋን የመፈተን አቅም አላት። በዚሁ ምድብ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ታንዛንያ ከደቡብ አፍሪካ በሆነር ስታዲየም ይጫወታሉ። ደቡብ አፍሪካ በሶስት ነጥብ ምድቡን እየመራች ነው። ታንዛንያ ያለ ምንም ነጥብ በአንድ የግብ እዳ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት ደቡብ አፍሪካ ካሸነፈች ሩብ ፍጻሜ ትገባለች። ታንዛንያ በውድድሩ የመጀመሪያ ድሏን ለማስመዝገብ ጠንካራ ተጋጣሚዋን መርታት ይኖርባታል። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ ተገናኝተው ደቡብ አፍሪካ ሶስት ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዛለች። በቀሪው ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። ደቡብ አፍሪካ በጨዋታዎቹ ስምንት ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ታንዛንያ ሶስት ግቦችን አስቆጥራለች።
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራዎች የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት እንዲረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው
Jul 12, 2025 13
አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በሀገሪቱ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢንሼቲቭ ሥራዎች የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት እንዲረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ በብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ገለጹ። የፌደራል እና የክልሎች የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊዎች ዛሬ በአርባ ምንጭ ጋንታ ተራራ ላይ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። በዚሁ ጊዜ በብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) እንደገለጹት በሀገራችን ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢንሼቲቭ ሥራዎች የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት እንዲረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። የአረንጓዴ ልማት ሥራው የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ፣ የከርሰ ምድር ውሃን በማጎልበትና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ነው ያሉት። በአርባ ምንጭ ጋንታ ተራራ ላይ ከአካባቢው አመራሮችና ነዋሪዎች ጋር በመሆን አረንጓዴ ዐሻራ በማኖራቸው መደሰታቸውን ገልጸው በዚህም ችግኝ ብቻ ሳይሆን የአንድነት፣ የአብሮነት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነትን ትርክት ጭምር ተክለናል ብለዋል። የተተከሉ ችግኞች አርባ ምንጭ ከተማን ከጎርፍ ከመታደግ ባለፈ ዓባያና ጫሞ ሐይቆችን ከደለል በመከላከል ለሐይቆች ህልውና ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ገልጸዋል። በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ሳሙኤል ኡቦያ በበኩላቸው የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት በክልላቸው የአካባቢን ስነ-ምህዳርና ብዝሃ ህይወት በመጠበቅ ጉልህ ጠቀሜታ እያስገኘ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአርባ ምንጭ ጋንታ ተራራ ላይ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጋራ የአረንጓዴ ዐሻራ ማኖራቸው አብሮነትን እንደሚያጠናክር ገልጸዋል። በብልጽግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ አሚና ኢብራሂም፣ የአረንጓዴ ዐሻራ የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ለማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ በአርባ ምንጭ ከተማ ጋንታ ተራራ ላይ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ዐሻራቸውን ማኖራቸው ይህንኑ የሚያጠናክር ነው ብለዋል። የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ(ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ ከተጀመረ ወዲህ የዞኑ የደን ሽፋን እንዲሁም ምርትና ምርታማነት እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። ዛሬ የተተከሉ ችግኞች ለአርባ ምንጭ ከተማ ህልውና ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኙ በመሆኑ በቀጣይ ህብረተሰቡን በማስተባበር እንደሚንከባከቡ ገልጸዋል። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት በአርባ ምንጭ ከተማ ዶይሳ ቀበሌ የአቅመ ደካማ እናት መኖሪያ ቤትን ሙሉ ወጪ በመሸፈን ዛሬ በአዲስ መልክ ግንባታ አስጀምሯል። የብልጽግና ፓርቲ ዋናው ጽህፈት ቤት የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ላይ በአርባ ምንጭ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል።
በክልሉ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ4 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዷል
Jul 12, 2025 32
አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ4 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ገለጸ። የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትልና የወጣቶች ዘርፍ ሃላፊ ማርቆስ ማቴዎስ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ ችግሮች መፍታት የሚያስችል ነው። በተያዘው የክረምት ወራት ከ4 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት በክልሉ 12 ዞኖች እና ሦስት ሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱም በወጣቶች በሚከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎች ሊወጣ የሚችል ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የህዝብና የመንግስት ሀብት ለማዳን ታቅዷል ብለዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የአረንጓዴ አሻራ ልማት፣ የአረጋውያንና አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እድሳትና ግንባታ እንዲሁም የጽዳትና ውበት ሥራዎችን ጨምሮ 14 የልማት ሥራዎች ተለይተው ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል። ክልል አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችን በማካሄድ የህብረተሰቡን የእርስ በርስ ትስስር ለማጠናከር ትኩረት መሰጠቱንም ጠቁመዋል። በክልሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር እያደገ መምጣቱን ጠቁመው ወጣቶች በልማት ሥራው በመሳተፍ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተናግረዋል። የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊ ወጣት ሰላም ሐጎስ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአዕምሮና የመንፈስ እርካታ ከመስጠት ባለፈ ለሀገርና ለወገን አስተዋጽኦ እንድናበረክት እያገዘን ነው ብላለች። በበጋ ወቅትም በተለያዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፎች መሳተፏን አስታውሳ በክረምቱም ይህን ተግባር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጻለች። የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ወጣቶች በልማት ሥራ በመሳተፍ ለሌሎች ወጣቶች አርአያ ለመሆን እያስቻለን ነው ያለው ደግሞ የጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ ነዋሪው ወጣት ስምኦን እንዳሻው ነው። ዝናብና ጸሐይ ሲፈራርቅባቸው የነበሩ አረጋውያንና አቅመ ደካሞችን ከችግራቸው መታደግ በገንዘብ የማይተመን ደስታ ይሰጣል ብሏል። በተያዘው ክረምት በሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የድርሻውን ለመወጣት ከጓደኞቹ ጋር ሆኖ ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ተናግሯል። በጌዴኦ ዞን የዲላ ከተማ ነዋሪ ወጣት ትዝታ ዘለቀ በበኩሏ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተሳተፈች መሆኑን ገልጻ፣ አገልግሎቱ በትውልድ መካከል ያለን ግንኙነት ከማጠናከር ባለፈ ስብዕናችንን በመልካም ለመገንባት እያስቻለን ነው ብላለች። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በጋሞ ዞን በአረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግበር ችግኝ በመትከል ባለፈው ረብዑ በይፋ መጀመሩ ይታወሳል።
በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እስካሁን 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ተተክሏል - ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)
Jul 12, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እስካሁን 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ መተከሉን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዘንድሮውን አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል። የግብርና ሚኒስቴር አመራርና ሰራተኞችም በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬታማነት የኢትዮጵያ ማንሰራራት እና የከፍታ ጉዞዋ አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ በዚህ ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በዚህ ዓመት የመትከል ስራ በሁሉም አካባቢ እየተከናወነ ነው ብለዋል። እስካሁን በተከናወነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርም 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ መተከሉን ሚኒስትሩ ጨምረው ገልጸዋል። የሸገር ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የግብርና ክላስተር አስተባባሪ ግርማ ኃይሉ በበኩላቸው፥ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የሸገር ከተማን ለማስዋብና በአካባቢ ጥበቃ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን የሚደግፍ መሆኑን ተናግረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማዋ የምክር ቤት አባላት አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኖሩ
Jul 12, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ የምክር ቤት አባላት በእንጦጦ ተራራ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል። ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል ታቅዶ በሁሉም አካባቢዎች የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እየተከናወነ ይገኛል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 874
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ። በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1288
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 957
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል። ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1584
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
የህንድ የፈጠራ ማዕከል - ባንጋሎሩ
Jul 2, 2025 394
ቤተልሄም ባህሩ(ኢዜአ) የዴልሂና አግራ ቆይታችንን ጨርሰን ወደ ቀጣይ መዳረሻችን ባንጋሎሩ ከተማ ልንጓዝ ስንሰናዳ አብዛኛው የጋዜጠኛ ልዑክ ያሳሰበው እንደሰም የምታቀልጠውን የአግራ ፀሀይና ሙቀት በባንጋሎሩም ታገኘን ይሆን? የሚለው ነበር። ሆኖም ከዴልሂ ኢንድራ ጋንዲ አየር ማረፊያ ተነስተን ለሶስት ሰዓት ከተቃረበ በረራ በኋላ ያገኘናት ባንጋሎሩ የተለየች ሆነን አገኘናት። ባንጋሎሩ ቀዝቀዝ ባለ አየር ነበር እንግዶቿን የተቀበለችን። በዕለቱ ከክፍሎቻችን ወጥተን በጋራ ወደአየር ማረፊያ የሚወስደንን ትራንስፖርት ስንጠባበቅ ከጋዜጠኛ ቡድኑ ስድስት አባላት ከአጠገባችን እንዳልነበሩ አስተዋልን። የት ጋር እንደተነጣጠልን አላስታውስም። በዚህ ምክንያት ግን የእለቱ ጉዟችን ተሰርዞ ከተማዋን ለማየት ስንዘዋወር የማውቀው ዓይነት እንጂ የተለየ ሙቀት አላስተናገድኩም። የ13 ወር ፀጋ በመባል የምትታወቀው አገሬ ኢትዮጵያ ከዳሎል እስከ ራስ ዳሽን ባላት የመልከዓ ምድር አቀማመጥና ልዩ ልዩ የአየር ጠባይ ሙቀቱንም፣ ቅዝቃዜውንም ማወቃችን እንደዚህ ለአለ አጋጣሚ መልካም ስሜት ይፈጥራል። በተወሰነ ደረጃ በህንድ ያጋጠመኝ የአየር ባህሪ ከአገሬ ጋር ቢመሳሰልብኝ የፈጣሪንና የተፈጥሮን ስራ አጃኢብ ብዬ እንዳልፍ አድርጎኛል። ባንጋሎሩ ከተማ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ማዕከል በመሆኗ የህንድ ሲልከን ቫሊ በመባል ትታወቃለች። ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ስፍራዎችም ከመገለጫዎቿ መካከል ናቸው። የጠፈር ጠበብቶቹ - ባንጋሎሩ ደርሰን በመጀመሪያ ያየነው ዓለም በስፔስ ሳይንስ እየሰራች ያለችውና እያስመዘገበችው የምትገኘው ውጤት ማሳያ የሆነውን የህንድ ስፔስ ምርምር ድርጅትን ነው። ተቋሙ የህንድ መንግስት የስፔስ ዲፓርትመንት አካል ሲሆን፤ ዶክተር ቪክራም ሳራብሃይ በተሰኙ ባለራዕይ በ1962 የተወጠነና አሁን ላይ በዘርፉ ተገዳዳሪ መሆን የቻለ ነው። የተቋሙ ዓላማ የስፔስ ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመተግበር ለተለያዩ አገራዊ ጥቅሞች ማዋል መሆኑን ተከትሎ የሳተላይት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማምረት ስራን ጨምሮ ከአገሩ አልፎ ለሌሎች አገራትም በዘርፉ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። የተደረገልን ገለፃ አብዛኛውን ጋዜጠኛ ያስደመመ ነበር ከገለፃ በኋላ በጋዜጠኞች የተነሳው ሃሳብም ህንድ በስፔስ ዘርፍ ያላት ልምድና ያከናወነችው ተግባር በቀጣይም ልትሰራ የወጠነቻቸው ሃሳቦች የአገሪቱን መዳረሻ የተለሙ በአገራቸው እንዲተገበር የሚናፍቁት መሆኑን ነው። ተቋሙ በዘርፉ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም ትብብሩን የሚያጠናክር መሆኑን ከተደረገልን ገለፃ ተገንዝበናል። በሳይንስ፣ ኢንጂነሪንግና አስተዳደር ምሁራንን በማስተማር እያበረከተ ያለው የህንድ የሳይንስ ኢንስቲትዩት በባንጋሎሩ ከጎበኘናቸው መካከል የሚጠቀስ ነው። ኢንስቲትዩቱ ከአፍሪካ የተውጣጡ ተማሪዎችን የሚያስተምርና ከተቋማት ጋርም በዘርፉ የሚሰራ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ከጅማ፣ በተግባር ለመቀየር ሲታትሩ የስታርት አፖችን የምርት ውጤቶቻቸውን ሲፈትሹና ሲሞክሩ ተመልክቻለሁ። በኢትዮጵያም አሁን ላይ ለስታርት አፖች በተሰጠው ትኩረትና በተፈጠረው ምቹ ስነ ምህዳር የፈጠራ ውጤቶች እያደጉና እየተበራከቱ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። እንደ አዳማና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተቋማት የተማሪዎችን ፈጠራ ወደ ውጤት ለመቀየር እየተጉ መሆኑና የስታርት አፕ ኤግዚቢሽንና የሰመር ቡት ካምፖች ፈጠራን ምን ያህል እያበራከቱ መሆናቸው በጉብኝቱ ወቅት ወደ አዕምሮዬ የመጣ የአገሬው ህዝብ በውጤት የታጀበ ጥረት ነው። ከአራት አስርት ዓመታት በላይ በባዩቴክኖሎጂ ዘርፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘው ባዮኮንም ከባላንጎሩ የጉብኝት መዳረሻችን መካከል የሆነና አስፈላጊ መድሀኒቶችን የሚያመርትና በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይም እየሰራ ያለ ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት የአቅም ግንባታ ስልጠናው ተጠቃሚ ናቸው። ከ120 በላይ በሆኑ አገራት ለስኳርና ካንሰር ህመም የሚያገለገሉ መድሀኒቶችን በማምረትና በማሰራጨት ለህሙማን ፈውስና ለጤናው ዘርፍ ስርዓት አስተዋፅኦ እያበረከተም ይገኛል። የተቋሙ ላቦራቶሪና ዘመኑን የዋጀና ደረጃውን የጠበቀ ማምረቻ ፋብሪካን መጎብኘቴ አለም በፋርማሲዩቲካልስ ዘርፍ ያለችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። የባንጋሎሩ ቤተመንግስት - ይህን ቤተ መንግስት ማስቃኘቴን ከመጀመሬ በፊት በስፍራው ካስገረመኝ ነገር ላወጋችሁ ወደድኩ። ቤተ መንግስቱን ለመጎብኘት ያቀናነው በእለተ ሰኞ ነበር። ሆኖም ምድረ ግቢውን ቃኝተን ስለህንፃው ሰምተን ከመመለስ ውጪ ወደ ውስጥ አልዘለቅንም። ለምን? ለሚለው ምላሹ በዚህ ስፍራ "ሰኞ የእረፍት ቀን ናት" ነው። እንዴት ካላችሁ ቤተ መንግስቱ ቅዳሜና እሁድ በበርካታ ሰዎች የሚጎበኝ መሆኑን ተከትሎ በስፍራው ለሚሰሩ ሰራተኞች የእረፍት ቀናቸው ሰኞ በመሆኑ ነው። የቤተ መንግስቱ ምድረ ግቢ ሰፊና ልምላሜ የተላበሰ ሲሆን፤ የሚያምርና ለዓይን የሚስብ ኪነ ህንፃ ያለው ነው። አሰራሩና ውጥኑም እንደሚከተለው ነው። በዎዲየር ስርወ መንግስት ንጉስ ቻማራጃ ዋዲያር ወደ እንግሊዝ ባደረጉት ጉዞ በለንደን ዊንሶር ግንብ ይደነቃል። ተደንቆም አልቀረ የባንጋሎሩ ቤተ መንግስትን በተመሳሳይ ሁኔታ ይገነባል። ይህ ቤተ መንግስት በተወሰነ መልኩ የመካከለኛው ዘመን የኖርማንሲና የእንግሊዝ ግንቦችን ይመስላል። ቪድሃና ሶውዳ የካራንታካ ህግ አውጪ አካል መናገሻ በጉብኝታችን ያየነው ሌላው መዳረሻ ስፍራችን ነው። የህግ አውጪና የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የያዘው ይህ ህንፃ ህንድ ነፃነቷን ካገኘች በኋላ በራሷ መሀንዲስ የሰራችው የመጀመሪያው ህንፃ መሆኑ ተገልፆልናል። የህንፃ ግንባታ ጥበብ ማሳያ፣ የፖለቲካ መናገሻ እንዲሁም የባህል ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። እንደአጠቃላይ በቆይታዬ የተመለከትኩት የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ማበረታቻ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራ ኢትዮጵያ እያከናወነች ካለው የኮሪደር ልማትና ስታርት አፕን የማበረታታት ብሎም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ምቹነት ስራዎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ነው። በህንድና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ዘመናትን የተሻገረ፤ ለሁለት ሺህ ዓመታት የዘለቀ መሆኑን የታሪክ መዛግብት ያሳያል። የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት በአክሱም ስርወ መንግስት ኢትዮጵያና ህንድ በአዱሊስ ወደብ በኩል የንግድ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። በወቅቱ ኢትዮጵያ ቅመማ ቅመምና ሐርን ከህንድ ትገበይ ነበር። ህንድ ደግሞ ወርቅና የዝሆን ጥርስን ከኢትዮጵያ ትሸምት ነበር። ህንድ ከንግድ ልውውጥ ባሻገር በኢትዮጵያ ኪነ ህንፃ ግንባታ ላይ አሻራዋን አኑራለች። በኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍም ትልቅ አበርክቶ ያላት አገር ናት። ህንድ ነፃነቷን ካገኘችበት እኤአ 1948 አንስቶ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት ኢትዮጵያና ህንድ ሌላው የሚያመሳስላቸው ነገር ሆኖ ያገኘሁት የአምራች ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እያከናወኑ ያሉት ንቅናቄ ነው። ህንድ እ.አ.አ ከ2014 ጀምሮ የአምራች ዘርፉን ለማበረታታት "ሜድ ኢን ኢንዲያ" በሚል ለአስር ዓመት የተገበረችውና በርካታ ለውጥ የተመዘገበበት ንቅናቄ በኢትዮጵያ ከ2014ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ካለውና የሃገር በቀል ምርቶች እና አምራቾችን ማጠናከር፣ የኢንዱስትሪያል ማህበረሰብ ግንባታን ማሳደግ ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢ መፍጠር እና የጥናት እና ምርምር ችግር ፈቺነትን ማሳደግን ዓላማ ካደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ጋር የተመሳሰለ ነው። ንቅናቄ በኢትዮጵያ መተግበሩ ዓመታዊ የዘርፍ ዕድገት፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና ገቢ ምርት በመተካት በኩል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑም ይታወቃል። በህንድ ተዘዋውሬ በተመለከትካቸው ከተማዎች ባሉ ጎዳናዎች ከታዘብኩት ነገር ሰዎች ከሱቅ ለሚገበያዩት ነገር ሳይቀር በዲጂታል መንገድ ክፍያ መፈፀማቸውን ነው። በባጃጅና በሞተር የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘትም ጭምር ሞባይሉን በመጠቀም “ይህ ቦታ የት ነው?” ሳይል ያሻዎት ስፍራ መድረስም ሌላው ትዝብቴ ነው። ይህ ነገር በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትኩረት አግኝተው እየተሰራባቸው ካሉት የዲጂታል ክፍያና ዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ መርሃ ግብር ጋር የሚመሳሰል ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በቆይታችን ልክ እንደአትሌቶቻችን ሁሉ በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርጎ የሚያስነሳውን ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዝናና ክብር ለማስተዋል ችያለሁ። ፀጉረ ልውጥ መሆናችንን የተገነዘቡ በገበያ ማዕከላት የሚያገኙን እንዲሁም በምንጎበኛቸው ተቋማት የምንተዋወቃቸው ህንዳውያን "ከየት ናችሁ?" ብለው ሲጠይቁ፤ ለእኔና አንድ ከሌላ መገናኛ ብዙሃን የሄድን "ከኢትዮጵያዊ" ስንል የሚከተልልን ምላሽ "አሃ የኢትዮጵያ አየር መንገድ" የሚል ነው። ይህም አየር መንገዱ ስሙ ከኢትዮጵያ ተሰናስሎ የሚጠራ የአገሪቷ መታወቂያ ተቋም መሆኑን ያስገነዘበኝ ነው። ከህንዳውያን ጋር ብቻ ሳይሆን አብረን ከተጓዝን ጋዜጠኞች አንዱ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእናንተ የብቻ ሳይሆን እኛንም እንደራሳችን ሆኖ እያገለገለን ያለ የጋራ አየር መንገዳችን ነው" ሲል ነው የገለፀው። ይሄ ለእኔ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገር ኩራት ብቻ ሳይሆን መለያ ምልክትም ጭምር መሆኑን የተረዳሁበት አጋጣሚ ነው። በቀናት ቆይታዬ በእንግዳ አክባሪነታቸውና በለገሱን ፍቅርና እንክብካቤ ከአገሬ የራቅኩ ያህል ሳይሰማኝ ብቸኝነትን ሳላስተናግድ እንደውም እየናፈኳቸው እንድመለስ ላደረጉኝ ህንዳውያን በከበረ ሰላምታ ላመሰግን እወዳለሁ።
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 435
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል። ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል። የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው። የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው። ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 966
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች። የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች። ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ። ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 1086
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 3337
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት
Dec 16, 2024 2786
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 2962
የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል። ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 4090
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2641
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2354
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3803
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል። በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል። የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
መጣጥፍ
ከሮም እስከ አዲስ አበባ
Jul 11, 2025 100
ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ይካሔዳል። የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ኢንቨስትመንት እና ፋይናንስ፣ የምግብ ስርዓት ሽግግር ሁለንተናዊነትና የተገቡ ቃሎችን ከመፈጸም አንጻር ያለውን የተጠያቂነት ስርዓት ማጠናከር ጉባኤው ትኩረት ያሚያደርግባቸው ሀሳቦች ናቸው። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተምግብ ጉባኤ በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በጣልያን ሮም የተካሄደው የመጀመሪያ የተመድ ስርዓት ምግብ ላይ የተገቡ ቃሎች ትግበራ ሂደትን መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ነው። በመጀመሪያው ጉባኤ ላይ የ182 ሀገራት ተወካዮች፣ 21 የሀገራት መሪዎች እና 126 ሚኒስትሮችን ጨምሮ 3 ሺህ 300 ተሳታፊዎች ታድመውበታል። በጉባኤው ላይ የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሀገራት እና ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ስድስት የትኩረት አቅጣጫዎችን ይፋ አድርገው ነበር። የምግብ ስርዓት ስትራቴጂዎችን ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር፣ ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓት አስተዳደር መገንባት፣ በጥናት፣ ዳታ፣ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ ሁሉን አቀፍ የእቅድ ዝግጅት እና ትግበራን ማጠናከር፣ በምግብ ስርዓት ውስጥ የንግዱ ማህበረሰብ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የአጭርና የረጅም ጊዜ የአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ ከትኩረት አቅጣጫዎቹ መካከል ይጠቀሳሉ። ኢንቨስትመንት፣ የበጀት ድጋፍ እና የእዳ አስተዳደር ሌላኛው የትኩረት መስክ ነው። በጉባኤው ላይ 300 ገደማ በሚሆኑ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የምግብ ስርዓት ሽግግርን እውን ለማድረግ ቃል መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃ ያመለክታል። በተለይም እ.አ.አ 2030 የማይበገር፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የምግብ ስርዓት መገንባት እንዲሁም ምግብ ለሁሉም የሚለውን ግብ ለማሳካት ጥረት እንደሚያደርጉ ሀገራት ቃል ገብተዋል። ሁሉን አሳታፊ ነው በሚል አድናቆት ያገኘው ጉባኤው በስርዓት ምግብ ላይ ግንዛቤን ከማሳደግ እና አቅምን ከመገንባት አንጻር ውጤታማ እንደነበር ይነሳል። የምግብ ስርዓት ሽግግር አንገብጋቢና ጊዜ የማይሰጥ ጉዳይ እንደሆነም በጉባኤው ተወስቷል። ኢትዮጵያም በስርዓተ-ምግብ ጉባኤው ላይ የነበራት ተሳትፎ ስኬታማ ነበር። በግብርናው ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ውጤታማ እንቅስቃሴዎችን የሚያሳዩ ልምደችን አቅርባለች። በጉባኤው ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ግብርናን በማዘመን የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥና በስርዓተ ምግብ ሽግግር ለማምጣት እየወሰደች ባለው የፖሊሲ እርምጃና ውጤቶች ዙሪያ ገለጻ አድርገውም ነበር። ኢትዮጵያ የኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት፣ ለየስነ ምህዳሩ ተስማሚ የሆኑ የተሻሻሉ ዝርያዎችን፣ አነስተኛ ቴክኖሎጂዎችንና ሌሎች ግብአቶችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለኢኮኖሚው ዕድገት የላቀ አበርክቶ እንዲኖረው እየሰራች መሆኑንም አንስተዋል። በአረንጓዴ አሻራ፣ በበጋ መስኖ በተለይም በበጋ ስንዴ ምርት እና በሌማት ትሩፋት እየተገኙ ያሉ ውጤቶችን ለጉባኤው አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግብርና ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የስራ እድል ፈጠራን ለማበረታታትም ሆነ በስርዓተ-ምግብ ሽግግር ለማድረግ አዲስና የተለየ የፋይናንስ ሞዴል ያስፋልጋል በማለት በአጽንኦት ተናግረዋል። ዘላቂና አካታች የስርዓተ ምግብ ሽግግር አቅጣጫዎች ጥሩ አፈጻጸም የታየባቸው ቢሆንም በፋይናንስ አቅርቦት፣ በዓለም አቀፍ ትብብር፣ በአየር ንብረት ለውጥና በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመቋቋም በትብብር በመስራት በኩል በርካታ ችግሮች መስተዋላቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የገለጹት። በመሆኑም ሀገሮች በስርዓተ ምግብ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በአነስተኛ እርሻ ስር-ነቀል ለውጥ በማምጣት ሽግግሩን ማፋጠን እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፅንኦት አንስተዋል። ለዚህም የሴቶችና የወጣቶች ተሳትፎን እንዲያሳድጉና ለግብርና ቴክኖሎጂ መስፋፋት እንዲሰሩ ጠይቀዋል ። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ-ምግብ ጉባኤ የመጀመሪያውን ጉባኤ መነሻ በማድረግ በተለያዩ አጀንዳዎች ይመክራል። ቀዳሚ ትኩረቱ ከመጀመሪያው ጉባኤው በኋላ የምግብ ስርዓትን አስመለክቶ ያሉ ለውጦች ምንድን ናቸው? የሚለው ነው። በጉባኤው ላይ ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን አስመልክቶ ያገኟቸውን ስኬቶች እና የጋጠሟቸው ተግዳሮቶች ላይ ሪፖርት ያቀርባሉ። በተለይም የምግብ ስርዓት ሽግግሩ ሁለንተናዊነት እና ሁሉን አሳታፊነት ዋንኛ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ሁለተኛው የጉባኤው አጀንዳ በመንግስታት፣ የምግብ አምራቾች፣ የንግድ ማህበረሰቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር ነው። የባለድርሻ አካላት ትብብር መጠናከር የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንዳለው ታምኖበታል። በተጨማሪም ሀገራት እና ተቋማት በሮሙ ጉባኤ የገቧቸው ቃሎች የደረሱበትን ደረጃ የሚገመገም ሲሆን ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎም ይጠበቃል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት እና የኢንቨስትመንት መጠንን መጨመር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ጉባኤው ይመክራል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር ስራዎች በአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ፣ አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም እና ሀገር በቀል የፋይናንስ መሰብሰብ አቅምን ማጎልበት ላይ ምክክሮች ይደረጋሉ ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ በሮም በነበረው ጉባኤው ላይ ይፋ ያደረጓቸው ስድስት የትኩረት መስኮች አፈጻጸም ግምገማ ሌላኛው አጀንዳ ነው። በአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባ የሚካሄደው ሁለተኛው የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ የሀገራት መሪዎች እና ተወካዮች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ አርሶ አደሮች፣ አምራቾች እና የምግብ ስርዓት ሽግግር ተዋንያንን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። በጉባኤው ላይ ከዋናው ሁነት ጎን ለጎን የምግብ ስርዓት ትራስፎርሜሽን እና የስርዓተ ምግብ ሽግግርን አስመልክቶ በርካታ የጎንዮሽ ስብስባዎች ይደረጋሉ። ኢትዮጵያ በምግብ ስርዓት ሽግግር ያከናወናቸውን ስራዎች አስመልክቶም በጉባኤው ተሳታፊዎች የመስክ ምልከታ ይደረጋል። ኢትዮጵያ በስርዓት ምግብ ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ እና በግብርናው ዘርፍ ባደረጋቻቸው ሀገር በቀል ሪፎርሞች ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ጉባኤውን እንድታስተናግድ የተመረጥችባቸው ምክንያቶች ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር እየተወጣች ያለው የመሪነት ሚና እና በማደግ ላይ ከሚገኙ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ተምሳሌት የሆነች ሀገር መሆኗ ተመድ ዓለም አቀፉን ከፍተኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ እንዲያደርግ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። በጉባኤው ላይ ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግርን ለማሳካት እያከናወነች ባለው ተግባር ዙሪያ ተሞክሮዋን ለዓለም ማህበረሰብ የማስገንዘብ ስራ ታከናውናለች። ተባባሪ አዘጋጇ ጣልያን እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ በምግብ ስርዓት ሽግግር ውጤታማ ተሞክሮ ያላት ሀገር ናት። የደቡብ አውሮፓዊቷ ሀገር ከኢትዮዮጵያ ጋር በመሆን ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን እየሰራችም ትገኛለች። ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ተሳታፊዎች ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እየጠበቀች ትገኛለች።
በቻይና ይህም አለ!
Jul 8, 2025 222
በአብነት ታደሰ በርግጥ ከዓለማችን የጥንት ስልጣኔ ምድሮች አንዷ ናት- ቻይና። በታሪክ ገጾች ‘የግኝት ምድር’(Land of Invention) የሚል ተቀፅላ የሰፈረላት የሺህ ዘመናት ባለታሪክ ሀገር። የጥንት ቻይኖች አያሌ ‘ግኝቶችን’ ለዓለም አካፍለዋል። ወረቀት ፈብርከው ዘመናቸውን ጽፈዋል፣ ማተሚያ ቁስ ፈጥረው አትመዋል፤ ኮምፓስ ፈልስመው አቅጣጫ ጠቁመዋል።በ221 ዓመተ-ዓለም አንድ ወጥ ስርወ መንግስት መስርተው በሀገረ መንግስት የታሪክ ዑደት ከፍታንም ዝቅታንም አይተዋል። በቻይና አያሌ ስርወ መንግስታት ተፈራርቀዋል። ቻይናውያን ክፉውንም ደጉንም ችለው አልፋዋል። የሕዝቡ ጽናት፣ ጥበብ፣ ቱባ ባህል፣ ታሪክና ብልሃት በቻይና ግንብ ይመሰላል። ግንቡም ዝም ብሎ የጡብ ክምር አይደለም፤ የመሰረተ-ጽኑነታቸው ትዕምርት(symbol) እንጂ። ሲሶውን ሕዝቧ በያንግትዝ ወንዝ ተፋሰስ ጉያ አቅፋ፣ ጥንተ ማንነቷን ሸክፋ ዕልፍ ዘመናትን ተሻግራለች። የቻይና ስርወ መንግስታት ከስመው የዛሬዋ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ ቻይና ከተመሰረተች ገና አንድ ምዕተ ዓመቷ ነው። ቅድመ ልደተ ክርስቶት በ221 ዓመተ-ዓለም የተመሰረተው ወጥ-ስርዎ መንግስት በመልከ ብዙ ምክንያቶች ተዳከመ። በፈረንጆቹ 1912 የመጨረሻው የቻይና ስርዎ መንግስት ተንኮታኮተ። ዘመናዊቷ የቻይና ሪፐብሊክ በዚህ ዘመን ተመሰረተች። ዳሩ ለውጡ አልጋ በአልጋ አልሆነም። ለሺህ ዘመን የጽኑ ስርዓተ መንግስት ባለቤቷ ሀገር ቻይና በአስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት ታመሰች። ወረራንም፣ ዕልቂትንም አስተናገደች። በዘመኑ ማኦ ዘዶንግ የሚባል ባለራዕይ መሪ በቻይና ምድር ተነሳ። አርቆ አሰበ፤ ሀሳቡንም አሰረጸ፤ በዓላማ ጸንቶ ክፉ ዘመን ተሻገረ። ማኦ እና ተከታዮቹ ለቻይና ትንሳኤ ታተሩ። በጽናት ታገሉ። ለመስዕዋትነት ቆርጠው ተነሱ፤ ዋጋም ከፈሉ። በአውሮፓዊኑ ዘመን አቆጣጣር በ1949 የዛሬዋን የቻይና ሕዝባዊ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ መሰረተ። ሃሳቡን ወደ ፖሊሲ ቀየረ፤ ተገበረውም። ቻይናን በኢንዱስትሪና ግብርና ምርት በንቅናቄ የማስፈንጠር ፕሮግራምንም (Great Leap Forward) ገቢራዊ አደረገ። ሆኖም ፖሊሲው በአንዴ ፍሬ አላፈራም። በወቅቱ በተፈጥሯዊና በሌሎች ምክንያቶች ቻይና በረሀብ ጠኔ ተመታች። ቻይናዊያን ተራቡ፤ ጎረቤት ሀገራትን ደጅ ጠኑ፤ ታላቁን ረሀብ መሻገር ያልቻሉ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቻይናዊያን በረሀብ አለቁ። በቻንግሻ የሚገኘው የማኦ ዘዶንግ ግዙፍ ሐውልት መራራ ጽዋን ተጎነጩ። የሀገሪቷ መሪ ማኦ ዘዶንግ በወቅቱ ፈተና ተስፋ ሳይቆርጥ ሀገር አሻጋሪ ፖሊሲውን ገቢራዊ አደረገ። ልመናን ለትውልድ ላለማውረስ፣ ንቅዘትን(ሙስናን) ነውር የሚያደርግ ስርዓት አጸና። ስራን ወንጌል፤ ሙስናን ወንጀል ያደረገ ጽኑ ስርዓተ መንግስት ገነባ። ከራሷ አልፋ ለዓለም የተረፈችዋን የዛሬዋን ቻይና በጽኑ መሰረት ላይ አነበረ። የዛሬዋ ቻይና ከዓለማችን ቁንጮ ልዕለ ሃያል ሀገራት አንዷ ናት። ከራሷ አልፋ ለዓለም ተርፋለች፤ የቻይና ቴክኖሎጂ ምጥቀትና ርቀት ዓለም ጉድ አሰኝቷል። በቅርቡ ሀገረ ቻይናን ከጎበኙ ጋዜጠኞች አንዷ ሆኜ ‘መልክዓ ቻይና’ን በወፍ በረር ቃኘሁ። በዚህ ማስታወሻዬ በቻይና የቴክኖሎጂ ልህቀትና ምጥቀት ላይ ብቻ አተኩራለሁ። ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ህዝብ ባላት፣ በ14 ሀገራት በምትዋሰነው፣ በአንድ ኮሚኒስት ፓርቲ በምትመራው ሀገር ቻይና በነበረኝ የ15 ቀናት ቆይታ ቻይና እንደ ጥንተ ታሪኳ ሁሉ በዘመኑ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ላይ ያላትን የመራቀቅ ጥግ ታዘብኩ። ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን የመቅደም እሽቅድድሟ ‘አጃይብ’ ያሰኛል። በሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና በማዕከላዊ ቻይዋ በምትገኘው የሁናን ግዛት ዋና ከተማ ቻንግሻ ምልከታዬ ቻይና ’ከተባለላት በላይ’ የቴክኖሎጂ ምጥቀቷ አስደንቆኛል። ምናልባትም የመጀመሪያ ጉዞዬ መሆኑም ነገሩን በአንክሮት እንድመለከት ሳያስገድደኝ አልቀረም። የሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከ22 ሚለዮን የሚልቅ ህዝብ በጉያዋ የታቀፈችው ታላቋ ቤጂንግ ከተማ ከዓለማችን ግንባር ቀደም የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህል፣ የቱሪዝምና የዲፕሎማሲ ማዕከላት አንዷ ናት። የአዲስ አበባ እህት ከተማ በዚህ ወቅት ሞቃታማ አየር ጸባት አላት። ቤጂንግ የ21ኛው ክፍል ዘመን የኪነ ህንፃና ክትመት ቴክኖሎጂ ያበበች ብቻ አይደለችም፤ ይልቁኑም በዛፎች ሀመልማላዊ ገጽታ የተላበሰች ውብ መዲና እንጂ። በሕንፃዎችም፣ በዛፎችም የተደነነች ከተማ። በተፈጥሮ የበቀሉ የሚመስሉ ሰማይ ታካኪ ሕንጻዎች፤ የመንገድ መሰረተ ልማት ስፋት፣ ጽዳትና ጥራት ‘ኩልል’ ያለች፣ ‘ምልል’ የምታደርግ ከተማ ያደርጋታል። ቤጂንግ ከተማ ከዘመናችን አስደናቂ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አንዱ በሆነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት(አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ) ሕይወትና ኑሮን እንዴት እንዳቃለለ የቤጂንግ የዕለት ከዕለት ክዋኔ ሁነኛ ማሳያ ነው። ቻይኖች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ተጠበዋል፤ መጠበብ ብቻም ሳይሆን ኑባሬያቸውን ሰው ሰራሽ አስተውሎት መር አድርገዋል። ከሮቦት መስተንግዶ እስከ ሰው ሰራሽ ፀሐይ መራቀቅ ይስተዋላል። ካረፍኩበት ሆቴል (15ኛ ወለል ላይ ከሚገኘው መኝታ ክፍሌ) ሆኜ ያዘዝኩት ምግብ በቅጽበት አስተናጋጇ ‘ከች’ ብላ ትደውላለች። ፍጥነቷ ስትገረም፤ አስተናጋጆች ሮቦቶች መሆናቸውን ስትመለከት ይበልጥ ትደነቃለለህ። በክፍሌ ውስጥ ማብሪያ ማጥፊያ ስጫን መጋረጃው ሲከፈት መደንገጤን አልሸሽግም፣ ከምሽቱ 3 ሰዓት ፀሐይ አለመጥለቋን ስመለከት ‘የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ወጣች እንዴ?’ ማለቴ አልቀረም። በነገራችን ላይ የቻይና የሰው ሰራሽ ፀሐይ ሳይንሳዊ ፈጠራ ሁለት ግዜ ተሞክሮ ያለምንም እንከን እንደሚሰራ ነግረውናል። የሰው ሰራሽ ፀሐዩ ሃይድሮጅን እና ዱተሪየም ጋዞችን እንደ ሀይል ማመንጫ ነዳጅነት በመጠቀም ንጹህ ኢነርጂን ለማመንጨት ታስቦ ዲዛይን እንደተደረገና ሰው ሰራሽ ፀሐይ በርሐን ከተፈጥሮ ፀሐይ 13 እጥፍ ያክል ሙቀት እንደሚያመነጭም ሰምተን ተደንቀናል። የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ፕሮጀክት የሥራ ሰዓትን ከ13 ሰዓት ወደ 24 ሰዓት ለመጨመርና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብ የሰነቀ ነው። በቻይና በሰዉ ቅርፅ የተሰሩ ሮቦቶች በእግር ኳስ ጨዋታዎች ተወዳጅነት አትርፈዋል። ቤጂንግ የሚገኘው ሂዩማኖይድ የተሰኘ የሮቦት ቡድን የሰራቸው ሮቦቶች አመርቂ ውጤት ከራቀው የሀገሪቷ እግር ኳስ ቡድን ይልቅ የሀገሬውን ቀልብ እንደሳቡ ይነገራል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት በታገዘ የሮቦቶች ውድድር አያሌ ቻይናዊያን ይታደማሉ። ሮቦቶቹ በጨዋታ መሐል ቢወድቁ በራሳቸውን ይነሳሉ፤ ቢጎዱም ከሜዳ የሚወጡበት ስርዓት ተዘርግቷል። የታላቋ ቻይና ሰዎች ቴክኖሎጂን ከችግር መፍቻነት ወደ መዝናኛነትም አልቀውታል። በሀገራችን እንደ አዲስ ቴክኖሎጂ በንግዱ ስርዓት ውስጥ እየተዋወቀ ያለው የፈጣን ምላሽ መለያ ወይም ኪው አር ኮድ(Quick Response code) በቻይና ዕለታዊ ከዋኔዎች ቅንጦት አይደለም። በቻይና ማንኛውም ግልጋሎት በዚህ በዲጂታል ስርዓት ይከወናል። እንደሌሎች ስልጡን ሀገራት ሁሉ በንክኪ የሚደረግ ገንዘብ ዝውውር ቀርቷል። በቤጂንግ ጎዳናዎች በኪው አር ኮድ(QR Code) በሚንቀሳቀሱ ሞተር ሳይክሎችን በየመንገዱ ተሰድረዋል፤ የፈለገ መንገደኛ ሳይክሎችን በመጠቀም ወደ ፈለገበት ስፍራ ተንቀሳቅሶ ክፍያውን በኪው አር ኮድ ከፍሎ ይሄዳል። ሌላውም እንዲሁ። በአዲስ አበባ መኖሪያ ሰፈሬ የነበሩ ሳይክሎኝ ከደጃችን ደብዛቸው እንደጠፋ ሳስብ በቻይኖች ብልሃት፣ ታማኝነትና የከተሜነት ልህቀት ቀናሁ። በርግጥ በቻይና ኪው አር(QR) ኮድ ለተገለገልንበት መክፈያ ብቻ ሳይሆን ለልመናም መዋሉን ሲመለከቱ ፈገግ ሊሉ ይችላሉ። በቻይና ይህም አለ በማለት። በርግጥ በቤጂንግ የሰው እጅ ከሚያይ ይልቅ ጆሮቸውን ቢቆጥርጣቸው የሚሰሙ የማይመስሉ አዛውንቶች ሳይቀር በስራ ላይ ተጠምደው ይስተዋላሉ። ከቻይናውያን ጋር ለመግባባት በተለይም በንግድ ማዕከላት የቻይንኛ ቋንቋ መረዳት ግድ ይላል። “ሃው ማቺ፣ ጉዳ ጉዳ፤ ሺሼ፣ ኢ፣ አር…” እና መሰል ቃላት ማወቅ ይበጃል። ከዚህ ባለፈ በምልክት መግባባት አልያም በቋንቋ ተርጓሚ መተግበሪያ መጠቀም ያሻል። የቻይና ሰራሽ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምርቶች በራሳቸው ብራንድ፣ ቋንቋና መልክ እየተመረቱ በተመጣጣሽ ዋጋ ለህዝቦቿ ተደራሽ እየተደረጉ ነው። የቻይና የራስ-በቅነት ጥረት ያስቀናል። በቴክኖሎጂ፣ በባሕልና በኢኮኖሚ ተጽዕኖ ተላቀው በራሳቸው ለመቆም የሄዱበት ርቀት ግሩም ነው። ግብይቶች በራሳቸው ገንዘብ ብቻ ይከወናል። በወቅቱ ምንዛሬ አንድ የአሜሪካ ዶላር ሰባት የቻይና ገንዘብ(ዩዋን) ነው። ከምዕራባዊያን ማህበራዊ ትስስር ገጾች(ለምሳሌ ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ፣ ቲክቶክ) በሕግ በማገድ የራሳቸውን መተግበሪያ አበልጽገው ገቢራዊ አድርገዋል። ‘ዊቻት’ የተሰኘው መተግበሪያ ሁሉም ቻይናውያን መገልገያ ነው። ከቤጂንግ ሌላ ያስደነቀችኝ ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከተማ ነች። ቻንግሻ ስመ-ብዙ ነች። ከሶስት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ ጠገቧ የሁናን ግዛት ርዕሰ መዲና ቻንግሻ ‘የከዋክብት ከተማ’ ትሰኛለች። በነገራችን ላይ ማኦ ዘዶንግ ትውልዱ ሁናን ግዛት ውስጥ ነው። ቻንግሻ በስራ ከተማነቷ ‘የማታንቀላፋው መዲና’ ትባላለች። በመዝናኛ ስፍራነቷ ‘የተዝናኖት መነሃሪያ’ የሚል ተቀጥላ ስም አላት። ‘የሚዲያ ጥበብ’ ስፍራም ትሰኛለች። በኢንዱስትሪ፣ በጥንታዊ ሐውልቶች፣ አብያተ መቅደሶች፣ ታሪካዊ ስፍራዎች መገኛ በመሆኗ በቱሪስቶች ተወዳጅ ከተማ ናት። ትናንትና ዛሬን ያዋደደች፣ ታሪክና ባህል ባዛነቀችዋ ቻንግሻ የአምስት ቀናት ቆይታዬ ብዙ ገጽታዋ አስደምሞኛል። የሻንግ ወንዝን ተንተርሳ፣ በተራራማ፣ በሜዳማና ኮረብታማ መልክዓ ምድር በማዛነቅ የተቆረቆረች በመሆኗ የስብት ማዕከል ሆናለች። እንደ ቤጂንግ በደን የተከበበች፣ በዘመነኛ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች እና በታሪካዊ ኪነ ሕንጻዎች የተጌጠች ከተማ ናት። ከዚህ ባሻገር የአምራች ኢንዱስትሪዎች መናገሻም ናት። የምቹ ከተሜነትና ጠንካራ የስራ ባህል በግላጭ የሚስተዋልባት ከተማ። የዓለማችን ገዙፉ በጣም ሞቃታማ አየር ጸባይ ባላት ቻንግሻ ሌት ከቀን ይሰራል። ፋብሪካዎቿ አይተኙም። ሌትና ቀኑ የሚታወቀው በሰዓት ብቻ እንጂ የስራና የንግድ ድባቡ እኩል ነው። ብርሃናማዋ ቻንግሻ ‘የቻይዊያን መስቀል’ በተሰኘው በቀይ በተቀለመው መስቀልም ትታወቃለች። በርግጥ ከዓለማችን ግዙፍ ማማዎች አንዱ የሆነው ሕንጻም መገኛ ናች። በጥቅሉ የቻይና ጉብኝት ትዝብቴ የገናና ታሪክ ባለቤቷ ሀገር ከባድ ውጣ ውረዶችን አልፋ ዛሬ ዓለምን እየቀደመች መሆኑን ሳስብ፤ እንደቻይና ሁሉ የሺ ዘመናት ገናና ታሪክና አኩሪ ገድል ያላት ኢትዮጵያስ የሚል ተጠየቅ እንዳውጠነጥን አድርጎኛል። ቻይናዊያን የዘመን የፈተና ቋጠሮዎቻቸውን ፈታተው ከዛሬ ከፍታ ሰገነት ላይ ወጥተዋል። ከዛሬም በበለጠ ነገን በጽኑ መሰረት ላይ እየገነቡ ነው። እኛስ? ብዬ ሳስብ በቁጭትና በተስፋ ተዋጥኩ! ሰላም!