ኢኮኖሚ - ኢዜአ አማርኛ
ኢኮኖሚ
በምዕራብ ወለጋ ዞን የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ነው
Mar 9, 2026 10
ጊምቢ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን ተግባራዊ የተደረጉ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ መምጣታቸውን የዞኑ አስተዳዳር ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ ለኢዜአ እንዳሉት በዞኑ በግብርና ዘርፍ ተግባራዊ የተደረጉ ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ናቸው። በዞኑ ከሰላም ማሰፈን ሥራ ጎን ለጎን የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰጠው ትኩረት በተለይ በሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ውጤታማ ሥራዎች እንደተከናወኑ ገልጸዋል። በመርሀግብሩ ተጠቃሚነት ለማሳደግም ዘንድሮ ከ116 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ለአርሶ አደሩ ለማሰራጨት ታቅዶ እስካሁን ድረስ 99 ሺህ 375 የንብ ቀፎ ተሰራጭቷል ብለዋል። በንብ ማነብ ሥራው 15 ሺህ አርሶ አደሮች መሰማራታቸውንና በዓመቱ መጨረሻም 12 ሺህ ቶን የማር ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን አቶ ተሊላ ጠቁመዋል። እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለጻ፣ ከንብ ማነብ ሥራ በተጨማሪ የወተት ላሞችን ዝርያ ለማሻሻል እና ለሥጋና እንቁላል ጣይ ዶሮዎች ስርጭት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። የሰብል ልማት ምርታማነትን ለማሳደግም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በግብርና ቴክኖሎጂ የመደገፍና የማስፋፋት ሥራ ተከናውኗል። በዞኑ ያለውን የመስኖ አቅም በማሳደግ አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት የማላቀቅና የሜካናይዜሽን እርሻ ልማትን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ተሊላ አመልክተዋል። በዘንድሮ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዞኑ ከ199 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ጠቁመው፣ ከዚህም 7 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል። የስንዴ ልማቱ በኩታገጥም እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት አቶ ተሊላ፣ ይህም አርሶ አደሮች ለሰብላቸው በጋራ ክትትልና እንክብካቤ በማድረግ የተሻለ ምርት እንዲገኝ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል። ከስንዴ ልማቱ በተጨማሪ ከ20 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ገበያ ተኮር የሆኑ አትክልቶች እየለሙ መሆኑንም አስረድተዋል። ከአትክልት ልማቱም 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው አቶ ተሊላ የገለጹት። በመስኖ ልማቱ ከ134 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸው፣ በዞኑ የተተገበሩ የግብርና ኢኒሼቲቮች የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትናና ሉአላዊነት እያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ በጊ ወረዳ ነዋሪ ሱሌማን ሞሐመድ እና ኑሩ ከላሜ በማህበር ተደራጅተው በሁለት ሄክታር መሬት ላይ በሚያከናውኑት ጥምር ግብርና ተጠቃሚ ሆነዋል። በመስኖ በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ አትክልቶች በማልማት ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመን የተቀረፁ ኢንሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው
Mar 9, 2026 52
አዳማ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመን የተቀረፁ ኢንሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ። የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማፋጠን አዳዲስ የምርምር ሥራዎች እየተካሄዱ ነው በአዲስ መልክ ተከልሰው ወደ ትግበራ የገቡ የወተት ልማት፣ ዶሮ፣ ዓሣና የእንስሳት መኖ ፓኬጆች ዙሪያ በየደረጃው ለሚገኙ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በአዳማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ ግብርናን ለማሻገር ከተቀረፁት ኢንሼቲቮች ውስጥ የእንስሳት ሀብት ልማትን የማዘመን ስራ አንዱ ነው። የእንስሳት ሀብቱን ውጤታማነት ለማሳደግና ዘርፉን ለማዘመን እየተተገበሩ ባሉ ኢኒሼቲቮች ተጨባጭ ውጤትና ለውጦች እየተመዘገቡ ናቸው ብለዋል። በዚህም የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ፣ የምግብና ስነ ምግብ ስርዓትን ለማስረፅ የሚደረገውን ጥረት የሚያሳኩ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን ገልፀዋል። የእንስሳት ዝርያን ለማሻሻል የተከናወኑት ተግባራት በተለይም በሰው ስራሽ ስነ ዘዴ በማዳቀል የወተት ሀብት ልማት እንዲጨምር ከማድረግ ባለፈ የተሻሻሉ ጥጆችና ጊደሮች በስፋት እንዲወለዱ ማድረጉን ነው የገለጹት። በየዓመቱም ከ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የወተት ላሞችን ማዳቀል እንደተቻለ አንስተዋል። ልዩ ዝርያ ያላቸውን የወተት ላሞችን በመደበኛና ሰው ሰራሽ ስነ ዘዴ ማዳቀልን ጨምሮ በዶሮ ፣ ዓሣና በማር ልማት ስራ የተሻለ ውጤት መምጣቱን አንስተዋል። የማር ልማት ኢንሼቲቭን ለማሳካት በየዓመቱ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎ እየተሰራጨ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የማር ምርት በዘመናዊ ቀፎ እንዲካሔድ መደረጉ ከባህላዊ ቀፎ ሲገኝ የነበረውን 10 ኪሎግራም የማይበልጥ ምርት በአማካይ 25 ኪሎግራም ለማድረስ መቻሉን ነው የተናገሩት። መድረኩ የእንስሳት ሀብት ዘርፉን ለማዘመን በተሰሩ ስራዎች የተገኙ ውጤቶችና ተሞክሮዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ግብርናን ለማሻገር የተቀመጠውን ግብ በተቀናጀ ርብርብ ለማሳካት ያለመ ነው ያሉት ደግሞ የቢሮው የእንስሳት ሀብት ልማት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ቶሌራ ደበላ ናቸው። በተጨማሪም የወተት ላሞች ልማት፣ የዶሮ፣ ዓሣ፣ ማር፣ ዓሣማና የእንስሳት መኖ ልማትን ጨምሮ በአዲስ መልክ የተከለሱ ስድስት ፓኬጆች ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥ አላማ ያነገበ ነው ብለዋል። ይህም የእንስሳት ሀብቱን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ፣ ምግብና ስነ ምግብ ስርዓትን ለማስረፅ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ እርምጃ ተወስዷል
Mar 9, 2026 62
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑ ተገለጸ። በክልሉ ኮንትሮባንድ እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቷል የክልሉ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አፀደ አይዛ በነገው እለት የሚካሄደውን የኢንቨስትመንት ፎረም አስመልክተው ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ ለማቅረብ በመቻሉ በርካታ ባለሃብቶችን ለመሳብ እየተቻለ መሆኑን አብራርተዋል። በተያዘው በጀት ዓመት 10 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 226 ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰደው ወደ ሥራ ገብተዋል ነው ያሉት። ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ እየተካሔደ ያለው የድጋፍና የክትትል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ኮሚሽነሯ የገለጹት። በአሁኑ ወቅትም ለኢንቨስትመንት መሬት ተረክበው ወደልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በተለዩ 81 ፕሮጀክቶች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ የተወሰደ ሲሆን 13 ሺህ 600 ሄክታር መሬት ወደ መሬት ባንክ ለማስገባት መቻሉን አስታውቀዋል። በነገው እለት የሚካሔደው የኢንቨስትመንት ፎረም ከባለሀብቶች ጋር ውይይቶችን በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያግዝ መሆኑን አመልክተዋል። በመሆኑም ባለሀብቶች በክልሉ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ በመጠቀም በኢንዱስትሪ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ለሎጎ ሐይቅ ሪዞርት መዳረሻነት የሚያገለግል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተፋጠነ
Mar 9, 2026 54
ደሴ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦በሐይቅ ከተማ አስተዳደር በሚገኘው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት እየተከናወነ ያለው የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ገለፀ። በክልሉ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማት ከዘርፉ የሚገኝን ገቢ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ በአካባቢው ለቱሪዝም ዘርፉ መነቃቃት እድልን ፈጥሯል። ሪዞርቱ የአካባቢውን ፀጋ ወደ ኢኮኖሚ ለመቀየር ከማገዙም ባለፈ ሀብቱን በዓለም ለማስተዋወቅ፣ ለዜጎች የሥራ እድል ለመፍጠርና ለከተማው እድገት አዎንታዊ ሚና እንዳለውም እሙን ነው። በሐይቁ አካባቢ እየተከናወኑ ባሉ የልማት ስራዎች ላይ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ከድር መሀመድ ለኢዜአ እንዳሉት፣ በከተማው በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎች ቢኖሩም ለምተው ጥቅም መስጠት ሳይችሉ ቆይተዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት መገንባትን ተከትሎ ለሪዞርቱ መዳረሻነት የሚያገለግል መሰረተ ልማት ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከተማ አስተዳደሩ በመደበው ከ150 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው በዚህም የብስክሌት፣ የእግረኛና ሌሎች መዝናኛዎች መካተታቸውን ተናግረዋል። እንዲሁም በፌዴራል እና በክልል መንግስት በጀት ከሐይቅ ከተማ በፒያሳ አደባባይ አድርጎ እስከ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት የሚወስደው ሁለት ነጥብ አንድ ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ ይገኛል ብለዋል። መንገዱ ደረጃውን የጠበቀ በግራና በቀኝ የእግረኛና የብስክሌት መንገድ ጭምር ያለው መሆኑንም አመልክተዋል። የሐይቅ ከተማ ነዋሪ አቶ አብዱ ሙሄ በበኩላቸው፣ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በከተማው ያሉ የታሪክ እና የገዳማት መገኛዎችን ለዓለም ያሳየ እና ለዘመናት የልማት ጥያቄዎች መልስ የሰጠ ነው ብለዋል። ሪዞርቱ የበለጠ የቱሪስት መዳረሻ እና ለጎብኚዎችም ምቹ እንዲሆን የአስፋልት መንገድና ሌሎችም የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን ገልፀዋል። የከተማዋን ሰላም በአንድነት በመጠበቅ ሪዞርቱ የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ በገንዘብና በጉልበት እያገዝን እንገኛለን ያለው ደግሞ ወጣት ሰይድ ዑመር ነው። ሪዞርቱ የተረሳውን የተፈጥሮ ፀጋ ወደ ሚጨበጥ ኢኮኖሚ የሚቀይር የልማት አሻራ በመሆኑ ተደስተናል ብሏል። የከተማው የኮሪደር ልማት እየተጠናቀቀ በመሆኑ ለሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ነው የገለጸው፡፡
በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ መስመር መልሶ ግንባታ እየተከናወነ ነው
Mar 9, 2026 57
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝ ለማድረግ 4ኛው ምዕራፍ የዲስትሪቢዩሽን መስመር መልሶ ግንባታና ዐቅም ማሳደግ ፕሮጀክት እየተከናወነ ነው። ሥራው እየተከናወነ የሚገኘው በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር ለኢዜአ ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ሥራው 703 ኪሎ ሜትር የዲስትሪቢዩሽን ኔትዎርክ መልሶ ግንባታና ዐቅም ማሳደግን ያካተተ መሆኑን አመላክተዋል። በተጨማሪም 2 ሺህ አዲስ የተለያየ ዐቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች ተከላና 2 ሺህ ነባር ትራንስፎርመሮችን ዐቅም የማሳደግ ሥራ የሚከናወንበት መሆኑን ጠቁመዋል። በፕሮጀክቱ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወጪ የሚሆኑ 56 ማሰራጫ መስመሮችን መልሶ የመገንባትና የማሻሻል እንዲሁም ከተፈቀደው የኃይል አጠቃቀም በላይ ሲሆን መቆጣጠር የሚያስችሉ 62 የሎድ ብሬክ ስዊች ገጠማ ይከናወናል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የፊዚካል ሥራ አፈፃፀም 36 ነጥብ 74 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፤ 2 ሺህ 857 የኮንክሪት ምሰሶዎች ተከላ ሥራም መከናወኑን አስታውቀዋል። ሥራው ሲጠናቀቅ በአዲስ አበባና በሸገር ከተሞች በዓመት በ100 ኪ.ሜ የመካከለኛ የኃይል ማሰራጫ መስመር ላይ የሚከሰተውን የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽን በ27 በመቶ ለመቀነስ ያስችላል ነው ያሉት። የትራንስፎርመር መቃጠልንም ወደ 2 በመቶ መቀነስ እንደሚያስችል አመላክተዋል።
የአየር ጤና - ካራ ወለቴ እና የአውቶብስ ተራ - መሳለሚያ 18 ማዞሪያ የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ በተፋጠነ ሁኔታ እየተከናወነ ነው
Mar 9, 2026 80
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦የአየር ጤና - ካራ ወለቴ እና የአውቶብስ ተራ - መሳለሚያ 18 ማዞሪያ የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ በተፋጠነ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ባለሀብቶችን በቀጥታ ማሳተፍ የሚያስችል ዘመናዊ የገበያ ስርዓት ተፈጥሯል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአየር ጤና - ካራ ወለቴ እና አውቶብስ ተራ - መሳለሚያ -18 ማዞሪያ የመንገድ ፕሮጀክቶችን የሥራ ሂደት ጎበኝተዋል። የአየር ጤና - ካራ ወለቴ የመንገድ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ ጥቂት ወራት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ከንቲባዋ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም አውቶብስ ተራ - መሳለሚያ - 18 ማዞሪያ የመንገድ ፕሮጀክት በመጪው ታህሳስ ወር ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ከንቲባዋ በጉብኝታቸው ወቅት እንደገለጹት፤ አውቶብስ ተራ - መሳለሚያ - 18 ማዞሪያ መንገድ ግንባታ ለረጅም ጊዜያት በተለያዩ እክሎች ምክንያት ተጓቶ የቆየ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን በተቀናጀና በፈጣን ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል። ፕሮጀክቱ 3 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን ባለ 6 መስመር መንገድ እንደሆነ ገልፀዋል። ዘመናዊ የመሿለኪያ መንገድ underpass የሚያካትት ሲሆን ሁሉም የፍሳሽ፣ የኤሌክትሪክና የውሃ መሠረተ ልማቶች በተቀናጀ መልኩ የተሟሉለት ነው ብለዋል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት በመጪው ታህሳስ ወር ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተያያዘም ከንቲባዋ የአየር ጤና - ካራ ወለቴ የመንገድ ፕሮጀክት የሥራ እንቅስቃሴን የጎበኙ ሲሆን ፕሮጀክቱ በተሻለ አፈፃፀም ላይ እንደሚገኝ ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል። ይህ ፕሮጀክት 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን የጎን ስፋቱ ደግሞ 40 ሜትር እንደሆነና ይህም የአካባቢውን የትራፊክ ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያቃልል ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ግንባታው በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንዳለ አንስተው በቀጣዮቹ ጥቂት ወራት እንደሚጠናቀቅም ተናግረዋል። የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቀንስና ለከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ መሳለጥ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይጠበቃል ብለዋል። በአጠቃላይ በከተማዋ 140 የመንገድ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ መሆናቸውን ተናግረው 104 የሚሆኑት በከተማው መንገዶች ባለሥልጣን በራስ አቅም እንዲሁም ቀሪዎቹ በግል ኮንትራክተሮች እየተገነቡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሙህዲን ረሻድ፤ መንገዶቹ በከተማዋ ኢኮኖሚ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው በመሆኑ በፍጥነት እና በጥራት እንዲጠናቀቁ ድጋፍ እና ከትትል እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
በሲዳማ ክልል በሞዴል መንደሮች ግንባታ የገጠሩን ማህበረሰብ ኑሮ ለማሻሻል የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Mar 8, 2026 157
ሀዋሳ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ሞዴል መንደሮችን በማስፋፋት የገጠሩን ማህበረሰብ ሕይወት ለማዘመን የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በመተባበር ያስገነባው ዘመናዊ የገጠር መንደር በሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና በፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ተመርቋል። በክልሉ ዳራ ወረዳ መጪሾ ቀበሌ የተገነባ ሞዴል መንደር አቅመ ደካማ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። በምረቃ መርሀግብሩ ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እንዳሉት በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ሞዴል መንደሮችን በማስፋፋት ህብረተሰቡ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ለማድረግ እየተሰራ ነው። በመንደሩ የተገነቡት ቤቶች ዘመናዊ ከመሆናቸው ባለፈ የስልጡን ማህበረሰብ መስፈርቶችን ያሟሉ በመሆናቸው ብልጽግናን በሁሉም አካባቢዎች ለማድረስ የሚደረጉ ጥረቶች ማሳያ ናቸው ብለዋል። የመደመር መንግሥት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን አንስተው የመጪሾ ሞዴል የገጠር መንደርም የዚሁ ጥረት ውጤት መሆኑን ገልፀዋል። በክልሉ ዛሬ ከተመረቀው በተጨማሪ የግንባታ ስራ የተጀመረባቸው ወረዳዎች እንዳሉና ተስፋፍቶ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ አቅም ከማሳደግ ባለፈ ዘመናዊ ሕይወት እንዲኖረው ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የገለጹት አቶ ደስታ፣ የሌማት ትሩፋትን ጨምሮ የግብርናን ምርታማነት ለማሳደግ በተሰራው ስራ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው ሞዴል መንደሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገጠር ኮሪደር ልማት እሳቤ በመነሳትና ቀደም ተብሎ ከተሰሩ ልማቶች ልምድ በመውሰድ የተገነባ መሆኑን ጠቅሰዋል። ቤቶቹ የውሃ፣ የፀሐይና የባዮ ጋዝ ኃይል ያላቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ የወተት፣ የዶሮና ሌሎች የሌማት ቱሩፋት ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችሉ ግንባታዎችን ያካተቱ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ሞዴል መንደሮቹ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር ወደዘመናዊነት ለመቀየር የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልፀው፤ በሁሉም አካባቢ መስፋት እንዳለባቸው አመልክተዋል። የመደመር መንግስት የገጠር አካባቢ ነዋሪዎችም ዘመናዊ አኗኗርን እንዲከተሉ በትኩረት እየሰራ ስለመሆኑ አንስተው በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በሞዴል መንደሩ አምስት ዘመናዊ ቤቶች የተገነቡ ሲሆን እያንዳንዳቸው በ1ሺህ 200 ካሬ ሜትር ላይ ያረፉ እንደሆኑም ተመላክቷል።
በክልሉ ኮንትሮባንድ እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቷል
Mar 8, 2026 141
አርባ ምንጭ ፤የካቲት 29/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንትሮባንድ እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት መሰጠቱን ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። የክልሉ ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር ግብረ-ሃይል የግማሽ ዓመት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንደገለጹት በክልሉ ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ በፈጠረው ምቹ ሁኔታ በገቢና ወጪ ንግድ ሥራ ላይ ሰፊ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል። ይሁንና ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎች በኢኮኖሚው ውስጥ ጤናማ ግብይት እንዳይካሄድ ዘርፈ ብዙ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይ ነዳጅን ጨምሮ በድጎማ የሚመጡ ሸቀጦችን ህዝቡ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንዳይጠቀም ጫና እያሳደሩ ይገኛሉ ብለዋል። እንደ አቶ ጥላሁን ገለጻ ጥራትና ብቃቱ ያልተረጋገጠ ህገወጥ ምርት ለማህበራዊ ቀውስ ከመዳረግ ባለፈ የተለያዩ ግጭቶች እንዲፈጠሩ በማድረግ ፖለቲካዊ ቀውስ ያስከትላል። በክልሉ የተቋቋመው የኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር ግብረ-ሃይል የተቀናጀ ቁጥጥር በማድረግ ጤናማና ፍትሃዊ የንግድ ሥርአት እንዲኖር ሃላፊነቱን እንዲወጣም አሳስበዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሰናይት ሰለሞን በበኩላቸው እንዳሉት በግማሽ ዓመቱ ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ መቆጣጠርን ጨምሮ በሁሉም ዘርፎች ውጤት ተመዝግቧል። ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የህግ የበላይነትን በመሸርሸርና ገበያን በማዛባት ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ስለሚያስከትል የመከላከል ሥራው በቅንጅት እየተከናወነ ነው ብለዋል። ባለፉት ስድስት ወራት የኑሮ ውድነት ለመፍጠር በሸቀጦችና ሌሎች ምርቶች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 21ሺህ 600 የንግድ ድርጅቶች ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱንም ተናግረዋል። ከነዳጅ ጋር በተያያዘ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያለው ነዳጅ በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ መያዙን የገለጹት ወይዘሮ ሰናይት፣ በነዳጅ ግብይት ህግ በተላለፉ 15 ማደያዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል። ግብረ-ሃይሉ ባደረገው ቁጥጥርም ከ910 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም 28 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መድሃኒትና ምግቦችን በመያዝ በህዝብ ላይ ሊደርስ የነበረን የጤና ችግር መቆጣጠር ተችሏል ብለዋል። በመድረኩ የክልል፣ የዞኖችና የከተሞች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና የፀጥታ አካላት የተሳተፉ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ላይም ውይይት ተደርጓል።
በክህሎትና ስነምግባር የታነፀ ትውልድ የማፍራቱ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
Mar 8, 2026 121
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በክህሎት፣ በእውቀትና በስነምግባር የታነፀ ትውልድ ለማፍራት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ። የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት በቦሌ አራብሳ አካባቢ ያስገነባውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤት ምረቃ እና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግንባታ ማስጀመሪያ መርሀግብር አካሂዷል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ በክህሎት የዳበሩ ህፃናትና ታዳጊዎችን ለማፍራት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ዛሬ የተመረቀው የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት በክህሎት በእውቀትና በስነምግባር የታነጸ ትውልድን ለማፍራት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልፀዋል። በክህሎትና በእውቀት የዳበረ ትውልድ የማፍራት ሀላፊነታችንን ሁላችንም ልንወጣ ይገባልም ብለዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በበኩላቸው፤ የትምህርት ስብራትን ለመጠገን በርካታ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ በትምህርትና ስልጠና ዜጎችን ወደ ላቀ እውቀት ለማሸጋገር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል። የኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤት ችግር ፈቺ የሆኑ ዜጎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። ትምህርት ቤቱ ታዳጊዎች በክህሎት የዳበረ እውቀት እንዲጨብጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል። መሰል ሞዴል ትምህርት ቤት መቋቋሙ ለሙያ ትምህርት የሚሰጠውን የተዛባ አስተሳሰብ ለማስተካከል ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል።
በክልሉ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው
Mar 7, 2026 94
ሀዋሳ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ላደረጉ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም ተካሄዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው። የክልሉ መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ስራ አጥ ዜጎችን ወደ ስራ ለማስገባት በሚደረገው ጥረት በክልሉ የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የፋይናንስና የክህሎት ስልጠና በመስጠት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የክልሉ መንግስት ከአጋር አካላት ጋር የጀመረውን ቅንጅት በማጠናከር በዘርፉ የሚከናወነውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ በበኩላቸው፤ በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ዘርፍ ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን በመተግበር ሂደት የክህሎት ልማት ላይ የተከናወኑ ተግባራት በዘርፉ ለተገኘው ውጤት ጉልህ ሚናን አበርክቷል ብለዋል። የስራ እድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ኢንዱስትሪውን እንዲቀላቀሉ በሚደረገው ጥረት የማምረቻና መሸጫ ቦታዎችን በማዘጋጀትና የማሽነሪ ድጋፍ መደረጉንም ተናግረዋል። የዛሬው መድረክ ዋና ዓላማም እስካሁን ለተከናወነው ተግባር ምስጋና በማቅረብ በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት ቅንጅቱን የማጠናከር ስራ ለመስራት ነው ብለዋል። በክልሉ የሚንቀሳቀሱ አጋር አካላት በተያዘው በጀት ዓመት ከ39 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስልጠና ድጋፍ ማድረጋቸውም ታውቋል።
በዞኑ ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ናቸው
Mar 7, 2026 130
ሆሳዕና ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በከምባታ ዞን ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ ፕሮጀክቶች የነበሩባቸውን ችግሮች በመቅረፍ ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድጉ መሆኑን የዞኑ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበልግ ወቅት ከ208 ሺህ 602 ሄክታር በላይ መሬት ይለማል የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በከምባታ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች የመስኖ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድና የተንጠልጣይ ድልድይ ፕሮጀክቶችን ግንባታ አጠናቆ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል፡፡ የዞኑ ነዋሪዎች በዚህ ወቅት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ ፕሮጀክቶች የነበሩባቸውን ችግሮች በመቅረፍ ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡ በዞኑ የሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር በለጠ ሾቢሶ፤ በአካባቢያቸው ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የሳቶራ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው በመስኖ ልማት እንዲሳተፉ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ከመደበኛ የግብርና ስራቸው በተጨማሪ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በወቅት ሳይገደቡ አልምተው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያሳድግም ገልጸዋል፡፡ በቃጫቢራ ወረዳ መሳፌ ቀበሌ ነዋሪው አርሶ አደር አስፋው አንሼቦ በበኩላቸው፤ በአካባቢያቸው የመንገድ መሰረተ ልማት ባለመኖሩ የሚያመርቱትን ምርት ለገበያ ለማቅረብም ሆነ ማህበራዊ አገልግሎት ለማግኘት ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ የክልሉ መንግስት ያጠናቀቀው መንገድ የጤና አገልግሎትን ጨምሮ የግብርና ምርታቸውን በቀላሉ ወደ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንደሚያደርጋቸውም ተናግረዋል፡፡ በአካባቢው የንፁህ ውጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በመኖሩ ከወራጅ ወንዝ በመጠቀም ለተላላፊ በሽታዎች ይጋለጡ እንደነበር የገለጹት ደግሞ በዞኑ የዶዮገና ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘሮ ብዙነሽ ኃይለ ማርያም ናቸው፡፡ በአካባቢው ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም የነበረባቸውን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት ሙሉ በሙሉ የሚቀርፍ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ እንደገለፁት፤ በክልሉ መንግስት የተገነቡት የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የመስኖ፣ የመንገድና የተንጠልጣይ ድልድይ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡ የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረግ የዞኑ ማህበረሰብ በሁሉም ዘርፍ ያለውን አቅም እንዲጠቀምና ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችለው ስለመሆኑም አመልክተዋል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በቅርቡ የተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡
የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማፋጠን አዳዲስ የምርምር ሥራዎች እየተካሄዱ ነው
Mar 7, 2026 135
አምቦ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማፋጠን አዳዲስ የምርምር ሥራዎችን እያካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለጸ። በክልሉ በቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመስኖ ልማት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ኢንስቲትዩቱ በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል የተሻሻሉ የወተት ላሞች ዝርያን ለሞዴል አርሶ አደሮች የማስተላለፍ እና የዕፅዋት ጥበቃ ምርምር ቤተ-ሙከራ ቁሳቁሶች የርክክብ ሥነ-ሥርዓት አካሂዷል። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ንጉሤ ደቻሳ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢንስቲትዩቱ የግብርናውን ዘርፍ ይበልጥ ለማዘመን የተለያዩ አዳዲስ የምርምር ሥራዎችን እያካሄደ ይገኛል። የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባለፈ፣ የሀገሪቱን እድገት ማፋጠን የሚችሉ በሳይንሳዊ ምርምር የተደገፉ ዘርፈ-ብዙ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለአብነትም በባዮ-ቴክኖሎጂ ሥራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር መደረጉን ገልጸዋል። በቀጣይም የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማፋጠን የሚያግዙ አዳዲስ የምርምር ሥራዎች በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥሉ መሆኑን አንስተዋል። የአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ጃማል ቶላ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የምርምር ማዕከሉ የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር መፍታት የሚችሉ የተለያዩ የግብርና ምርምር ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ጠቅሰዋል። ከተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) ድጋፍ የተገኘ የዕፅዋት ጥበቃ ምርምር ቤተ-ሙከራ ቁሳቁሶችን ኢንስቲትዩቱ ለአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ማስረከቡንም አስታውሰዋል። የቤተ-ሙከራ ቁሳቁሶቹ የዕፅዋት በሽታዎችን ለመለየትና የአካባቢውን አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚረዱ ተናግረዋል። ለብዙ ዓመታት የምርምርና ብዜት ሥራ ሲከናወንባቸው የነበሩ የተሻሻሉ የወተት ላሞች ለሞዴል አርሶ አደሮች ተላልፈው መሰጠታቸውን የተናገሩት ደግሞ በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል የጊንጪ መለስተኛ ግብርና ማዕከል ዳይሬክተር ተስፋዬ አበራ (ዶ/ር) ናቸው። ማዕከሉ የወተት ላሞቹን ካስተላለፈ በኋላም አርሶ አደሮቹን በአንድ መንደር በማደራጀት አስፈላጊውን ሙያዊ ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እንደሚሠራም ገልጸዋል። የአካባቢው አርሶ አደሮችም የተሻሻሉ የወተት ላሞች ዝርያ በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው፤ ለላሞቹ አስፈላጊውን ጥበቃ በማድረግ ገቢያቸውን ለማሻሻልና በሀገራዊ እድገት ውስጥ ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የአምቦ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር አቶ ወልደሰማያት ለታ፤ ከግብርና ሥራቸው ጎን ለጎን የወተት ላሞቹን በማርባት ከሚያገኙት ምርት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ገቢያቸውን ለማሳደግ እንደሚሠሩ ተናግረዋል።
የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎች እየተዘረጉ ነው
Mar 7, 2026 190
አዳማ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በዘላቂነት ለመጠበቅና የዘርፉን አሰራር ለማዘመን የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎችን እየዘረጋ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ገለጸ። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና የኢትዮጵያን የንግድ ምህዳር ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታላቅ ዕድል ነው ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የረቂቅ ደንቡን ይዘት በባለድርሻ አካላት ግብዓት ለማዳበር ያለመ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል። የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በህግ ለመደገፍ አዋጅ ቁጥር 1376/2018 ወጥቶ ወደ ሥራ እንዲገባ ተደርጓል። ይህም የሀገሪቱን የእንስሳትና የእንስሳት ውጤቶች የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳለጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው አሰራር ለመዘርጋት ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል። አምባሳደር ድሪባ አክለውም፤ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና ምርቱን የሚረከቡ ሀገራት የሚቀበሏቸው የህግ ማዕቀፎች ተዘጋጅተዋል ብለዋል። አሁን ላይ በእፅዋትና በእንስሳት ዘርፎች አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ስታንዳርዶች ፀድቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የህግ ማዕቀፎቹ የዘርፉ ኢንዱስትሪዎች፣ በተለይም የስጋ አምራቾች ፍላጎትን መሰረት ያደረጉና ከዓለም አቀፍ አሰራር ጋር የተናበቡ እንዲሆኑ ታስቦ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የባለሥልጣኑ የሬጉላቶሪ ዘርፍ ዳይሬክተር ሃሚድ ጀማል (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባለፉት ሰባት ወራት የእንስሳት ምርት ለማምረት ፈቃድ የተሰጣቸውን ተቋማት ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የአሰራር ማሻሻያዎች መደረጋቸውን ገልጸዋል። ምርት ወደ ውጭ ከመላኩ በፊት ከማምረቻው ጀምሮ ጥራትና ደህንነቱ መጠበቅ እንዳለበት ያመለከቱት ዳይሬክተሩ፤ ምርት በቁምም ሆነ ታርዶ ለተጠቃሚው ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ እንዲላክ ተቋሙ ከግብርና ሚኒስቴርና ከባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የባለሥልጣኑ የእንስሳት ምርት ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አያሌው ሹመት በበኩላቸው፤ የህግ ማዕቀፎቹ የኤክስፖርት ዘርፉን ማነቆዎች የሚቀርፉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ይህም የቁም እንስሳት፣ ስጋ፣ ዶሮ፣ እንቁላል፣ ዓሣ፣ ወተትና የማር ምርቶችን የቁጥጥር አሰራር የሚያዘምን መሆኑን ጠቅሰዋል። በህግ ማዕቀፎቹ ዝግጅት ወቅት የዓለም ንግድ ድርጅትን ጨምሮ የናሚቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ፣ ቦትስዋና፣ እንግሊዝና የብራዚል ምርጥ ተሞክሮዎች እንዲካተቱ አድርገናል ሲሉም ገልጸዋል። የህግ ማዕቀፎቹ ተግባራዊ መሆን ለሀገሪቱ የወጭ ንግድ ውጤታማነት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረውም ተመላክቷል።
በክልሉ በቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመስኖ ልማት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል
Mar 7, 2026 165
ጂንካ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመስኖ ልማት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2018 ዓ/ም ግማሽ ዓመት የስራ አፈፃፀሙን በጂንካ ከተማ እየገመገመ ነው። የቢሮው ኃላፊ ኤካል ነትር በወቅቱ እንደገለፁት፤ ቢሮው በቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት መለወጥ የሚያስችሉ የተቀናጁ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ነው፡፡ በተለይም ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ ቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የመስኖ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል፡፡ የአየር ንብረት ተፅእኖውን በመቋቋም የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ከሚተገበሩ ፕሮጀክቶች መካከል የመስኖ ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም በቆላማ አካባቢዎች ሰፋፊ የመስኖ አውታሮችን በመገንባት አርብቶ አደሩ በግብርና ልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን መደረጉን ገልጸዋል። በመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራትም የአንድ ከፍተኛ እና የሁለት መካከለኛ ግድቦች የግንባታ ስራ መጀመሩን ጠቁመው፥ ወደ 8 የሚሆኑ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ደግሞ በተያዘው ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በተያዘው ዓመት ከሚጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መካከል የአርጎባ፣ ብላቴኤታ፣ ማርቃላሾ፣ ሎማቴ እና ሳላ የተሰኙ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ በአካባቢው በመስኖ የማልማት ፍላጎት እያደገ በመምጣቱ አርብቶ አደሩና ከፊል አርብቶ አደሩን ያማከለ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ማስፋፋት የሚያስችል የጥናትና ዲዛይን ስራ እየተሰራ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል። ከመስኖ ልማት ባሻገር በግጦሽ ሳር ከለላ፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ፣ በንፁህ መጠጥ ውሃና በመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በእንስሳት ግብይት ማዕከላት ግንባታና በሌሎች ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ቦሼ ቦምቤ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቢሮው በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን ገልፀዋል። አርብቶና ከፊል አርብቶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በዘላቂነት ኑሮውን ለማሻሻል የተጀመረው የመስኖ ልማት እንዲጠናከር የክልሉ መንግስት በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡ በተለይ በግንባታ ላይ ያሉ የመስኖ ፕሮጀክቶች በአጭር ጊዜ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የተቀናጀ ርብርብ እንደሚደረግም ተናግረዋል። የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አብረሃም አታ በበኩላቸው፤ በዞኑ ቆላማ አካባቢዎች የተጀመሩ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች የከፊል አርሶ አደሩን ምርታማነት በማሻሻል በግብርና ልማት ተጠቃሚነቱ እንዲያድግ አድርጓል ብለዋል። የመስኖ ልማት መተግበር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ዓመቱን ሙሉ ለማልማት አቅም በመፈጠሩ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንዳስቻለም ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለቀጣናው ልማትና ሰላም መረጋገጥ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው
Mar 7, 2026 148
ሮቤ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን የሚያስተሳስሩ ግዙፍ የልማት ስራዎችን በማካሄድ ለቀጣናው ሰላም መረጋገጥ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር በሃሳብ ልዩነታችን ውስጥ የማንደራደርበት ቀይ መስመራችን ነው - የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ብሔራዊ ጥቅምን ያስከበረ ለአፍሪካ ቀንድ እና አጎራባች ሀገራት ትብብር፣ የጋራ ብልፅግና፣ ሰላምና መረጋጋት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰላምና የልማት አቅም በመሆን ረገድ ያለችበትን ሁኔታ በማስመልከት ኢዜአ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንን አነጋግሯል። አስተያየታቸውን የሰጡ ምሁራንና ተመራማሪዎች እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ከማስከበር ባለፈ ለቀጣናው ብልፅግና የጋራ ተጠቃሚነት መርህ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን አመልክተዋል። በዩኒቨርሲቲው የጂኦግራፊና አካባቢ ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ ፈዬ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ የሰላምና የልማት አቅም እየሆነች መምጣቷን ተናግረዋል። በተለይ የአፍሪካ ቀንድ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ለንግድ እንቅስቃሴ ምቹ መሆኑን ተናግረዋል። ቀጣናው ጥቂት የማይባሉ አካላት ፍላጎት ያለበት መሆኑንና ኢትዮጵያም ብሔራዊ ጥቅሟን በሚያስጠብቅ መልኩ ከሀገራት ጋር በትብብር እየሰራች መሆኑ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በመተባበር ቀጣናዊ ትስስርን የማጠናከር ጽኑ አቋሟን በተግባር እየገለጠች መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የስነ ዜጋና ሥነ ምግባር ትምህርት ክፍል መምህርና የቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር ጉተማ አደም ናቸው። ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በማከናወን ከራሷ አልፎ ለአካባቢው አገራት የጋራ ልማትና ተጠቃሚነት እየሰራች መሆኑን አመልክተዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ ለህዝቧ ፍላጎትና ተጠቃሚነት ይበጃሉ ብላ የምትወስዳቸው የተለያዩ እርምጃዎች ከሷ አልፎ ለቀጣናው ልማትና ሰላም መረጋገጥ የሚጠቅሙ በመሆናቸው የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣ እያስቻላት ስለመሆኑም አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በብሪክስ ባለ ብዙ ወገን የትብብር መድረክ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከራሷ አልፎ የአፍሪካን ድምጽ እያሰማች መሆኑን ያብራሩት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንትና ኢኮኖሚክስ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር ሁሳ አሎ ናቸው። ከዚህ አንፃር የኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ የልማት ጥረት በቀጣናውም ይሁን በአህጉሩ የስኬት መንገድ ውስጥ ትልቅ ድርሻ አለው ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በተለይም በኃይል፣ በትራንስፖርት እና በሌሎች መሠረተ ልማቶች ለማስተሳሰርና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እያደረገች ያለው ጥረት በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ እንደሚያጠናክርም አክለዋል።
የጅግጅጋ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለንግድና ኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጋት ነው
Mar 7, 2026 118
ጅግጅጋ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ የጅግጅጋ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ምቹ የመኖሪያ አካባቢ ከማድረግ ባለፈ ለንግድና ኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጋት መሆኑን ነዋሪዎች ተናገሩ። በአዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በክልሎችም እየተስፋፋ ስማርት፣ ምቹና ዘመናዊ ከተሞችን እውን የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል። ፕሮጀክቱ የከተማችን ብቻ ሳይሆን የሀገራችን ኩራትና ገጽታን የሚቀይር ስኬት ነው -ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለአኗኗርና ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበሩ ከተሞች በኮሪደር ልማት የብስክሌትና እግረኛ መንገዶችን ጨምሮ የመዝናኛ እና የመጫወቻ ስፍራዎችን በማካተት እየተሰሩ ይገኛሉ። በዚህ የልማት እቅድ ተጠቃሚ ከሆኑ ከተሞች መካከል በምስራቅ ኢትዮጵያ በንግድ እንቅስቃሴዋ የምትጠቀሰው ጂግጂጋ ከተማ አንዷ ነች። የጂግጂጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ታሪካዊ ይዘቷ ሳይለቅ፣ ዘመናዊነትን ከባህላዊ እሴቶች ጋር በማሰናሰል የከተማዋን ውበትና መልካም ገጽታ መግለጥ አስችሏል። በዚህም የከተማዋን የንግድ እንቅስቃሴ ይበልጥ ለማሳለጥና የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያስቻለ ዘመን ተሻጋሪ የልማት አሻራ መሆኑን ብዙዎች ይናገራሉ። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ አህመድ ቡራሌ ፋራህ፤ የኮሪደር ልማቱ በተከናወነባቸው የከተማዋ አካባቢዎች ለንግድም ይሁን ለመዝናኛ ምቹ ሆነው አግኝተናቸዋል ብለዋል። የእግረኛ፣የብስክሌት እና የተሽከርካሪዎች መንገድ ተለይተው መገንባታቸውን አንስተው በዚህም የትራፊክ አደጋን ለመከላከልና ለሰዎች ነፃ እንቅስቃሴ መልካም እድል ፈጥሯል ሲሉ ተናግረዋል። ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሱልጣን አብዲ ከሊፍ፤ የጂግጂጋ ከተማ ለውጥ አስደናቂ እና አስደማሚ መሆኑን ገልጸው መንግስትን አመስግነዋል። ለአካባቢው ከተሞች የልማት ተምሳሌት በመሆን የንግድና የኢንቨስትመንት ልማትን እና የቱሪዝም እንቅስቃሴን ለማሳለጥ የሚያስችል የከተማ ልማት እየተከናወነ ስለመሆኑ አንስተዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ተሌህ ደይብ፤ በጂግጂጋ ከተማ የኮሪደር ልማት በተጨማሪ በከተማዋና አካባቢው የሰይድ መሀመድ አብድሌ ሀሰን ሚሞሪያል ፓርክ እና ሌሎችም የመስህብ ስፍራዎች በአጭር ጊዜ በላቀ ጥራት ተገንብተው መጠናቀቃቸው አስደንቆናል ብለዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጣው ለውጥ በተለይም ለሶማሌ ክልል ልዩ እድል የፈጠረ መሆኑንም አንስተዋል። በከተማዋ የተሠሩና እየተሠሩ ያሉ መዝናኛ ፓርኮች ከተለያዩ አከባቢዎች የሚመጡ እንግዶች እና የከተማዋ ነዋሪዎች ለመዝናናት ምቹ እድል የሚፈጥሩ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል፤ ለዚህም ድጋፍና ትብብራችን አይለይም ሲሉ አረጋግጠዋል። በከተማዋ የተጠናቀቁ እና በሂደት ላይ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ትልቅ ተስፋ የሰነቅንባቸው ናቸው ያሉት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ መሀመድ ኢብራሂም ናቸው። በከተማ ልማቱ ለዘመናዊ አኗኗር እና ለጉብኝት ምቹ አካባቢ ከማድረግም ባለፈ ለንግድና ኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጋት ይገኛል ብለዋል።
በዞኑ በፍራፍሬ ልማት የተገኘውን ውጤት የበለጠ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Mar 7, 2026 133
ነቀምት ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ወለጋ ዞን በፍራፍሬ ልማት የተገኘውን ውጤት የበለጠ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በክልሉ የምርጥ ዘር አቅርቦትን በውስጥ አቅም ለመሸፈን በመቻሉ ለበልግ እርሻ ምቹ ሁኔታን ተፈጥሯል በጽሕፈት ቤቱ የቡና፣ አትክልትና ፍራፍሬ ቡድን መሪ አቶ አሰፋ መኮንን ፤ በዞኑ ለፍራፍሬ ልማት የሚመች የግብርና መሬት እንዳለ ለኢዜአ ገልጸዋል። በዚህም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለልማቱ በተሰጠው ትኩረት የፍራፍሬ ልማት ሥራ በስፋት እየተተገበረ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ለዚህም የዞኑ አርሶ አደሮች ከመደበኛ የሰብል ልማት በተጓዳኝ አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ እና ሌሎችንም የተመረጡ የፍራፍሬ ዓይነቶች እንዲያለሙ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በዞኑ ያለውን ምቹ ሥነ-ምህዳር፣ የአየር ንብረት እና በቂ የውኃ ሀብት በመጠቀም እስካሁን 15 ሺህ 371 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ ፍራፍሬዎችን ማልማት መቻሉን አስታውቀዋል። የፍራፍሬ ምርት እየለማበት ከሚገኘው ሄክታር መሬት ውስጥ ከፊሉ ምርት መስጠት መጀመሩን ጠቅሰው፤ በ2017/2018 ምርት ዘመን ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ተሰብስቦ ለገበያ መቅረቡን አብራርተዋል። የፍራፍሬ ምርቱ በአመዛኙ በጉደያ ቢላ፣ ጎቡ ሰዮ፣ ሲቡ ስሬ እና ጉቶ ጊዳ ወረዳዎች የተመረተ ሲሆን፤ የልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች የፍራፍሬ ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ገልጸዋል። የፍራፍሬ ልማቱን ለማስፋፋት የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ ተግባራዊ መደረጉን አንስተው፤ በየደረጃው በሚገኙ ችግኝ ማፍያ ጣቢያዎችም የፍራፍሬ ችግኞች በተደራጀ መልኩ በጥራትና በብዛት እየተዘጋጁ ለልማቱ ተሳታፊዎች ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን አውስተዋል። በምስራቅ ወለጋ ዞን ጎቡ ሰዮ ወረዳ ከልማቱ ተሳታፊዎች መካከል አርሶ አደር ስዒድ ጂላሉ በሰጡት አስተያየት፤ ባላቸው አንድ ሄክታር ይዞታ ላይ አቮካዶና ሙዝ በማልማት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። የፍራፍሬ ምርታቸውን ከሀገር ውስጥ ገበያ ባለፈ መንግሥት ባመቻቸላቸው የገበያ ትስስር በመጠቀም ካለፈው ዓመት ወዲህ 33 ኩንታል አቮካዶ ወደ ውጭ ሀገር በመላክ 150 ሺህ ብር ትርፍ ማግኘታቸውን ገልጸዋል። ከሙዝ ልማት ጋር በተያያዘም በስፋት ሥራ ውስጥ መግባታቸውን ጠቅሰው፤ አሁን ላይ የደረሰ ሙዝ በመሰብሰብ ለገበያ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል። ሌላኛው በዞኑ ጉቶ ጊዳ ወረዳ አርሶ አደር ሀብታሙ ደጀኔ በበኩላቸው፤ በየዓመቱ ከሚያመርቱት አቮካዶ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በፊት በሰብል ምርት ላይ ብቻ በመሰማራት የሚያገኙት ገቢ ውስን እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ግን ባገኙት ምርጥ ዘር እና ድጋፍ በመጠቀም ለውጭ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህ ዓመት በግማሽ ሄክታር መሬት ላይ 20 ኩንታል አቮካዶ ምርት በመሰብሰብ ለገበያ ማቅረባቸውን አውስተዋል። እንደ አርሶ አደሮቹ ገለጻ የአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት የተሻለ ገቢ ከማስገኘት ባለፈ የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ሥርዓተ ምግብ ለማሻሻል አስችሏቸዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ለሀገራዊ ደህንነትና ለቀጣናዊ ሰላም መከበር ወሳኝ ነው
Mar 7, 2026 70
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ሀገራዊ ደህንነትን ለማረጋገጥና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር ወሳኝ መሆኑን የቀድሞ የባህር ኃይል አባልና የታሪክ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተገቢና ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያለው ችግር በዘላቂነት እንዲፈታ ጥረት እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያና ቀይ ባህር ለዘለዓለም ተነጣጥለው እንደማይኖሩ በማንሳት፥ ፍትሐዊ ጥያቄያችን በሰላማዊ፣ በሰጥቶ መቀበልና በድርድር መርህ ምላሽ እንዲያገኝ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ ፍትሐዊ ካልሆነ በዓለም ላይ ፍትሕ የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የጊዜ ጉዳይ እንጂ መልስ ማግኘቱ አይቀሬ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የቀድሞ የባህር ኃይል አባል ጁኒየር ሌተናንት ሀለፎም መሰለ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ በሴራ የባህር በር አልባ እንድትሆን ከመደረጓ በፊት በአካባቢው ላይ ጠንካራና ተፅዕኖ ፈጣሪ የባህር ኃይል ነበራት። በዚህም በቀይ ባህር ቀጣና የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የሌሎች ሀገራት የንግድ መርከቦች ጭምር ደህንነታቸው ተጠብቆ ሰላማዊ ጉዞ እንዲያደርጉ ሀገሪቱ ወሳኝ ሚና ስትጫወት መቆየቷን አስታውሰዋል። የባህር ኃይሉ በተለይም ሕገ-ወጥ ንግድ፣ ኮንትሮባንድን፣ የባህር ላይ ሽፍቶችን እንቅስቃሴዎች በመግታት ለቀጣናው ሰላምና ደህንነት ዋስትና ሆኖ መቆየቱን ገልጸዋል። በሀገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የህልውና ጉዳይ ለሆነው የባህር በር ጥያቄ ዘላቂ ምላሽ ለማግኘት ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ እንዳለውም ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር በማጣቷ ምክንያት ከፍተኛ ዋጋ የከፈለች መሆኑን ጠቅሰው፤ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቀደም ብሎ ሊነሳ የሚገባው እንደነበር አንስተዋል። የታሪክ ምሁርና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር አህመድ ዘካሪያ በበኩላቸው፤ የጥንቶቹ የዳማትና የአክሱም ሥልጣኔዎች ከባህር በር ጋር በነበራቸው ቁርኝት የገነኑ እንደነበሩ በታሪካዊ ማስረጃነት ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለሷ ሀገራዊ ተጽዕኖዋን ከመጨመሩ በላይ ብሔራዊ ጥቅሟን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ጉልህ አሻራ እንደሚያሳርፍ አክለዋል። የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አደም ካሚል በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ድልና በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ያሳዩትን ጽኑ አንድነት የባህር በር ጥያቄው ግቡን እንዲመታና ብሔራዊ ጥቅሟ እንዲከበር በአንድነት በመቆም ሊደግሙት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በክልሉ የግብርና ልማት ስራዎችና የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ ተመራጭ የሥራ እድል መፍጠሪያ ሆነዋል
Mar 7, 2026 79
ዲላ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ልማት ስራዎችና የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ ተመራጭ የሥራ እድል መፍጠሪያ እየሆኑ መምጣታቸውን የክልሉ የሥራና ክህሎት ቢሮ ገለጸ። አካባቢያዊ አቅምን በአግባቡ መጠቀም ለዘላቂ መፍትሔ ትልቅ መሰረት ነው በጌዲኦ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች በሌማት ትሩፋት፣ በማኑፋክቸሪንግና ተኪ ምርቶች የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የስራ እንቅስቃሴ ምልከታ ተካሄዷል፡፡ በወቅቱም የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በክልሉ የግብርና ልማት ስራዎችና የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ ተመራጭ የሥራ እድል መፍጠሪያ እየሆኑ ነው፡፡ በተለይ ለክህሎት መር የሥራ እድል ፈጠራ በተሰጠው ልዩ ትኩረት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት አዋጭ በሆኑ ዘርፎች ወጣቶችን በማሰልጠን ወደ ሥራ እንዲገቡ በተደረገ ጥረት ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። በክልሉ በገጠር ወረዳዎች ስድስት ሄክታር እንዲሁም በከተማ አንድ ሄክታር መሬት ለሥራ ፈላጊ ወጣቶች በማቅረብ መሰረታዊ የሥራ እድል ፈጠራ ግቦች መሳካታቸውንም ገልጸዋል። በክልሉ የግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ አዋጭና ተመራጭ የሥራ እድል ፈጠራ ዘርፍ መሆኑን አንስተው በግማሽ ዓመቱ ብቻ በተለያዩ ዘርፎች ከ163 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች የሥራ እድል መፈጠሩንም ተናግረዋል። በቀጣይም የአካባቢውን ጸጋ መሰረት ያደረገ የስራ እድል በመፍጠር የኢንተርፕራይዞችን ልማት ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ እና የመስክ ምልከታውም የዚሁ አካል ነው ብለዋል። በዞኑ ባለፉት 6 ወራት ወደ 11 ሺህ ለሚጠጉ ወጣቶች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ያነሱት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ናቸው። በተለይ የአካባቢውን ጸጋ መሰረት በማድረግ ሰፊ መሬት በማይጠይቁ የሌማት ትሩፋት ዘርፎች ወጣቶችን ወደ ስራ ለማስገባት መቻሉን ጠቅሰው በዚህም ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል። ኢቶስ የወተት ላሞች እርባታና የመኖ ግብርና ኢንተርፕራይዝ ስራ አስኪያጅ አቶ ተካልኝ ዓለማየሁ በበኩላቸው፤ ከዛሬ ሶስት ዓመት በፊት በዲላ ከተማ በሁለት የወተት ላሞች የጀመሩት እርባታ ዛሬ ላይ ከ12 በላይ መድረሱን ተናግረዋል። ከአንዲት ላም በአማካይ ከ18 ሊትር በላይ ወተት እንደሚያገኙ አንስተው ይህንንም ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከወተት አቅርቦት ባለፈ በሶስት ሄክታር መሬት ላይ መኖን በዘመናዊ መንገድ በማልማት ለወተት ላሞቹ ከመመገብ አልፈው ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። በወተት ላም፣ በዶሮ እርባታና በማር ልማት በተቀናጀ ግብርና ተሰማርተው ውጤታማ መሆናቸውን ያሱት ደግሞ በወናጎ ወረዳ መኮኒሳ ቀበሌ የበጸሎት የተቀናጀ ግብርና ኢንተርፕራይዝ ስራ አስኪያጅ ሀገረ ሰላም በርሱ ናቸው። የእንስሳት ተዋጽኦዎችን በተለይ ወተትና እንቁላል እንዲሁም ዶሮ ለአርሶ አደሮች በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በዞኑ የሌማት ትሩፋት ተሳታፊዎች ምርታቸውን ከፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል
Mar 7, 2026 69
ጊምቢ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በመሳተፍ ምርታቸውን ከቤተሰብ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉ መሆኑን በምዕራብ ወለጋ ዞን ቤጊ ወረዳ የሚገኙ ወጣቶችና ሴቶች ገለጹ። በዞኑ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሳደግ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት በበኩሉ በበጀት ዓመቱ መርሃ ግብሩን ለማስፋፋትና ለማጠናከር ከ3 ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችና ቄብ ዶሮዎች፣ 100 ሺህ የሚጠጋ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ማሰራጨቱን አስታውቋል። በቤጊ ወረዳ የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች መካከል እስራኤል ብሩሴና ዮሐንስ ዘሪሁን ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በማህበር ተደራጅተው በሌማት ትሩፋት የተሻሻሉ የወተት ላም ዝርያ በማርባት ተጠቃሚ ሆነዋል። እንደ ወጣቶቹ አስተያየት እያረቧቸው ካሉት የተሻሻሉ አምስት የወተት ላሞች በቀን ከ50 ሊትር በላይ ወተት ያመርታሉ። ምርቱንም ከቤተሰብ ፍጆታ ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የተሻለ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። በተለይ የወተት ምርቱን በወረዳው ለሚገኙ ሆቴሎች፣ ካፌዎችና ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ስለሚያቀርቡ የገበያ ችግር እንዳላጋጠማቸው ገልጸው ከሽያጩም በወር በአማካኝ ከ25 ሺህ እስከ 30 ሺህ ብር የተጣራ ትርፍ እንደሚያገኙ አስረድተዋል። ገቢያቸውን በመቆጠብና ሥራቸውን በማስፋፋት ለሌሎች የአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ዕቅድ እንዳላቸውም አስታውቀዋል። በቤጊ ወረዳ የኮቦር ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ዘነበች ዲቢሳ በኩላቸው፤ በሌማት ትሩፋት የዶሮ ጫጩት ማሳደግ እና ማከፋፈል ሥራ ላይ በማህበር ተደራጅተው ወደ ሥራ መግባታቸውን ይናገራሉ። በከተማ አስተዳደሩ በተደረገላቸው የሼዶች ድጋፍ አሁን ላይ አንድ ሺህ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ተረክበው በማሳደግ ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው በቀጣይ እንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማርባት ተጠቃሚነታቸውን ለማስፋት እየሠሩ መሆናቸውን አብራርተዋል። የምዕራብ ወለጋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ሀምቢሳ፤ በዞኑ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተግባራዊ በመሆኑ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አስተዋፅኦ ከማበርከቱ ባለፈ ለብዙዎች የኢኮኖሚ ምንጭ በመሆን በተጨባጭ ውጤት ማስገኘቱን አውስተዋል። ጽሕፈት ቤቱ ልማቱን ለማጠናከርና ለማስፋፋት የዶሮ ጫጩቶች፣ የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸው የወተት ላሞችና የንብ ቀፎ ለመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች ማቅረቡን አመልክተዋል፡፡ በዚህ ረገድ በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ በዶሮ እርባታ ለተሰማሩ ነዋሪዎች 3 ሚሊዮን 250 ሺህ በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችና ቄብ ዶሮዎች፣ 100 ሺህ የሚጠጋ ዘመናዊ የንብ ቀፎ መሰራጨቱን ገልጸዋል። ከዚህ በፊት የተሰራጩ የተሻሻሉ ጊደሮችን በሰው ሠራሽ ዘዴ በማዳቀልም 24 ሺህ ጥጆች ተወልደው እንክብካቤ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ አብራርተዋል።