ሳይንስና ቴክኖሎጂ - ኢዜአ አማርኛ
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ከኦራክል እና ቪዛ ኩባንያ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ
Jun 2, 2023 43
አዲስ አበባ ግንቦት 25/2015 (ኢዜአ):-የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶክተር) ከአሜሪካው ዓለም አቀፍ የኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ ኦራክል ኩባንያ እና ከቪዛ የፋይናንስ አገልግሎት ኩባንያ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። በሞሮኮ ማራካሽ ከግንቦት 23 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ(ጂአይቴክስ) ዛሬ ማምሻውን ተጠናቋል። በአውደ ርዕዩ ላይ ከመላ ዓለም የተሰባሰቡ ታዋቂ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እና ጀማሪ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች የታደሙባቸው አውደ ርዕዮች እና አውደ ጥናቶች ተካሄደዋል። በመድረኩ የተሳተፉት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶክተር) እና ልዑካናቸው ከመድረኩ አውደ-ርዕዮች እና የስማርት አፍሪካ አውደ ጥናት ተሳትፏቸው ጎን ለጎን ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይቶችን አድርገዋል። በአውደ ርዕዩ ማጠናቀቂያ ላይ ሚኒስትሩ ከኦራክል እና ከቪዛ ኩባንያዎች የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል። ዶክተር በለጠ በውይይቱ በኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሂደት ላይ ማብራሪያ መስጠታቸውንና ኩባንያዎቹ በዲጂታላይዜሽን ስራዎች እና አገልግሎቶች ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸው ተመላክቷል። መንግስት ለዘርፉ እድገት አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ እና ለኩባንያዎቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አስረድተዋል። የኩባንያዎቹ ኃላፊዎች በበኩላቸው የኢትዮጵያ በዲጂታል ገበያ እድል ውስጥ ለመሳተፍ ፍላጎትና እቅድ እንዳላቸው መግለጻቸውን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ድርቅ በአርብቶ አደሩ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገለጸ
Jun 2, 2023 63
ቡሌ ሆራ ግንቦት 25/2015 (ኢዜአ):- የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ድርቅ በአርብቶ አደሩ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስታወቀ። የተፈጥሮ ሃብት አጠባበቅ ስራዎችን ከማጠናከር ባለፈ አማራጭ የውሃ አጠቃቀም ስርዓት በመዘርጋት ችግሩን ለመቅረፍ መሰራት እንደሚገባም ተገልጿል። የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ”አርብቶ አደርና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽኖ” በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው ሶስተኛውን ዓለም አቀፍ የጥናት እና ምርምር አውደ ጥናት እያካሄደ ነው። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ፍቃዱ ወልደማርያም እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን በግብርና፣ በጤና፣ማዕድን እና አገር በቀል እውቀቶች የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ ነው ብለዋል ። በተለይም በጉጂ እና ቦረና ዞኖች የአየር ንብረት ለውጥ በግብርና ልማቱ እና በእንሰሳት እርባታ እያደረሰ የሚገኘውን ጉዳት ለመቀነስ ዘርፍ ብዙ ጥረቶች እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በተለይ ምርምርን መሰረት ያደረገ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እንዲጠናከር እንዲሁም በቆላማ አካባቢዎች የሚገኘውን ዝቅተኛ የውሃ መጠን በአግባቡ ለመጠቀም በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል ። አውደ ጥናቱ በዘርፉ ዓለም አቀፍ የእውቀትና የልምድ ልውውጥ በማድረግ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት ያግዛል ነው ያሉት ዶክተር ፍቃዱ። የአፍሪካ የአከባቢ ጤና ማህበር ፕሬዝዳንት ዶክተር ተዋበች ቢሻው በበኩላቸው በአየር ንብረት ለውጥ ችግር የሚፈጠረውን የውሃ እጥረት ከእርባታ ስርዓቱ እና የገበያ ትስስር ውስንነት ጋር ተዳምሮ በኢትዮጵያ የእንስሳት ሀብት ላይ ጫና እያሳደረ ነው ብለዋል። የተፈጥሮ ሀብት አጠባበቅ ስራዎችን ከማጠናከር ባለፈ አማራጭ የውሃ አጠቃቀም ስርዓት በመዘርጋት ችግሩን ለመቅረፍ መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል። በዚህ ረገድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጥናት እና ምርምር ከማድረግ ባለፈ የጥናት ውጤትን መሰረት ያደረገ ትግበራ በማከናወን የበኩላቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ተናግረዋል። በአውደ ጥናቱ ላይ ምሁራን፣የአገር ውስጥ እና የውጭ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲሁም የመንግስት እና የግል ድርጅቶች ተሳታፊ መሆናቸው ተገልጿል። እስከ ነገ በሚቆየው አውደ ጥናት ከ40 በላይ የጥናት ውጤቶች ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
አገልግሎቱ ለተጠቃሚዎች በድምፅ፣ በምስልና በሌሎችም አማራጮች አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መተግበሪያ ይፋ አደረገ
Jun 1, 2023 57
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ለተጠቃሚዎች በድምፅ፣ በምስልና በሌሎችም አማራጮች አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መተግበሪያ ይፋ አደረገ። የተቀናጀ የቤተ-መጻሐፍት የቤተ-መዛግብትና ሪከርድ ማኔጅመንት (ኢላርም) መተግበሪያ በ31 ሚሊዮን ብር ወጪ በአንድ ዓመት የተከናወነ ፕሮጀክት መሆኑም ታውቋል። የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዳይሬክተር ይኩኖ አምላክ መዝገቡ መተግበሪያው (ሶፍትዌሩ) ለፈጣን አገልግሎት ተደራሽነት የላቀ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። የበርካታ መጻሕፍቶችና ሰነዶች ሃብት ባለው ቤተ መጽሃፍት ተጠቃሚዎች የሚፈልጉትን መጻሕፍት፣ በድምፅ፣ በምስልና ሌሎችንም አማራጮች በመተግበሪያው የተቀላጠፈ አገልግሎት የሚያገኙ መሆኑን ገልጸዋል። የአገልግሎቱ የኢንፎርሚሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር ኤልሳቤጥ አሸናፊ፤ የመተግበሪያው እውን መሆን የሪከርድና ማኅደር ክፍል በደንብ ተደራጅቶ አገልግሎት እንዲሰጥም ያግዛል ብለዋል። በዚህም የቤተ-መጻሕፍቱን ካታሎጎች ማንኛውም ሰው ባለበት ስፍራ ሆኖ በሚጠቀምበት ዌብሳይት ፖርታል በመግባት ማግኘት እንደሚችል ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በ1936 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ለቤተመጻሕፍቱ ባበረከቱት መጻሕፍት ሥራ መጀመሩን መረጃዎች ያመለክታሉ።
የስምጥ ሸለቆ ምዕራፍ 3 ግድብ የግንባታ ጥናት የውል ስምምነት ተፈረመ
Jun 1, 2023 82
ሀዋሳ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ)፡- ከ44 እስከለ 50 ሜጋ ዋት በላይ ሀይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል የተባለለት የስምጥ ሸለቆ ምዕራፍ 3 መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት የጥናትና ዲዛይን ስራ የውል ስምምነት ተፈረመ። በኦሮሚያ ክልል በቦረና በደቡብ ክልል ደቡብ የኮንሶ ውሃ አጠር አካባቢወች በሰገን ወንዝ ላይ ተንተርሶ የሚገነባው ግድቡ ሃይል ከማመንጨት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሏል። የፕሮጀክቱ አሰሪ መስሪያ ቤት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጥናቱን ከሚያካሂደው ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽንና ቁጥጥር ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር በሀዋሳ ስምምነት ተፈራርመዋል። በስምምነቱ ላይ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ እንዳሉት ውሃ አጠር በሆነው የቦረናና ኮንሶ አዋሳኝ አከባቢዎች በሚገኝ ተፋሰስ በሰገን ወንዝ ላይ መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመገንባት ዕቅድ ተይዟል። ሀገራችን የኤሌክትሪክ ሃይልን በተለያዩ አማራጮች እያሰፋች ትገኛለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም ለታዳጊ ኢኮኖሚያችን የሃይል አቅርቦት አማራጭ ወሳኝ መሆኑን ከግንዛቤ በማስገባት በትኩረት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል። ግንባታ ለማካሄድ የቅድመ አዋጭነትና አዋጭነት ጥናት ለማካሄድ የውል ስምምነት የተፈረመው የስምጥ ሸለቆ ምዕራፍ 3 መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክት ከ44 እስከ 50 ሜጋ ዋት በላይ ሃይል ለማመንጨት የታሰበ መሆኑን አስረድተዋል። ፕሮጀክቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዲኖረው ተደርጎ እንዲጠና የታሰበ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ ከ26 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በመስኖ የማልማት አቅም ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱን ተከትሎ የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ሎጆችና ሌሎች የመዝናኛ አማራጮችም ኮንሶና አከባቢው ላይ የሚታወቀውን የቱሪዝም ፍሰት ይበልጥ በማስፋት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማጠናከር ይረዳል ተብሎ መታሰቡንም አብራርተዋል። እንደ ሀገር ሃይል ማመንጨትና የአቅርቦት ስራዎች በአብዛኛው በጊቤና አባይ ተፋሰስ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አንስተው በዚህም የተፈጥሮ ሆነ መሰል አደጋዎች ቢከሰት ሊመጣ የሚችለውን ጫና አስቀድሞ ለመከላከል የተፋሰስ አጠቃቀማችንና የሃይል ስብጥር ከፍ ለማድረግ የሚያግዝ ነው ብለዋል። ግንባታው የሚካሄድበት የሰገን ወንዝ ፍሰቱ በሀገር ውስጥ ብቻ በመሆኑ ስራውን ለማከናወን ምቹ አጋጣሚ መሆኑም ተናግረዋል። ከ60 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚካሄደው የቅድመ አዋጭነትና የአዋጭነት ጥናት በሚቀጥሉት 18 ወራት የሚካሄድ ነው የተባለው። ጥናቱ እንደተጠናቀቀም ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና የግል አልሚዎች ተረክበው ወደ ግንባታ እንዲገቡ እንደሚደረግ ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። ግንባታውን የሚያካሂደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽንና ቁጥጥር ስራዎች ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ተሾመ ሲዳላ ግድቡ በሚያርፍበት አከባቢ የሚኖረውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ላይ ጥናት እንደሚደረግ ተናግረዋል። በውሉ መሰረት የባለሙያዎች ስብጥርና ልምድ በመጠቀም የቅድመ አዋጭነትና የአዋጭነት ጥናቱን በ18 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በፊርማው ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የደቡብ ክልል ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ በበኩላቸው በክልሉ የሚነሱ የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሰጠው ዕድል አመስግነዋል። በዛሬው ዕለት የተፈረመው የሃይል ማመንጫ ግንባታ ስራው አካባቢው በስምጥ ሸለቆ ያለና ውሃ አጠር በመሆኑ በተደጋጋሚ የሚከሰትን ድርቅ ከመከላከል አንጻር ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው ነው ያሉት። የጥናት ስራው በተገቢውና በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በክልሉ የሚገኙ ባለሙያዎችና ባለ ድርሻ አካላትን በማቀናጀትና ማህበረሰቡን በማሳተፍ ጠንካራ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል በቦረና በደቡብ ክልል ደቡብ የኮንሶ ውሃ አጠር አካባቢወች በሰገን ወንዝ ላይ ተንተርሶ የሚገነባው ግድቡ ከ44 እስከ 50 ሜጋ ዋት ሃይል ከማመንጨት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሏል። የፕሮጀክቱ አሰሪ መስሪያ ቤት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጥናቱን ከሚያካሂደው ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽንና ቁጥጥር ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር በሀዋሳ ስምምነት ተፈራርመዋል። በስምምነቱ ላይ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ እንዳሉት ውሃ አጠር በሆነው የቦረናና ኮንሶ አዋሳኝ አከባቢዎች በሚገኝ ተፋሰስ በሰገን ወንዝ ላይ መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመገንባት ዕቅድ ተይዟል። ሀገራችን የኤሌክትሪክ ሃይልን በተለያዩ አማራጮች እያሰፋች ትገኛለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም ለታዳጊ ኢኮኖሚያችን የሃይል አቅርቦት አማራጭ ወሳኝ መሆኑን ከግንዛቤ በማስገባት በትኩረት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል። ግንባታ ለማካሄድ የቅድመ አዋጭነትና አዋጭነት ጥናት ለማካሄድ የውል ስምምነት የተፈረመው የስምጥ ሸለቆ ምዕራፍ 3 መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክት ከ44 እስከ 50 ሜጋ ዋት በላይ ሃይል ለማመንጨት የታሰበ መሆኑን አስረድተዋል። ፕሮጀክቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዲኖረው ተደርጎ እንዲጠና የታሰበ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ ከ26 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በመስኖ የማልማት አቅም ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱን ተከትሎ የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ሎጆችና ሌሎች የመዝናኛ አማራጮችም ኮንሶና አከባቢው ላይ የሚታወቀውን የቱሪዝም ፍሰት ይበልጥ በማስፋት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማጠናከር ይረዳል ተብሎ መታሰቡንም አብራርተዋል። እንደ ሀገር ሃይል ማመንጨትና የአቅርቦት ስራዎች በአብዛኛው በጊቤና አባይ ተፋሰስ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አንስተው በዚህም የተፈጥሮ ሆነ መሰል አደጋዎች ቢከሰት ሊመጣ የሚችለውን ጫና አስቀድሞ ለመከላከል የተፋሰስ አጠቃቀማችንና የሃይል ስብጥር ከፍ ለማድረግ የሚያግዝ ነው ብለዋል። ግንባታው የሚካሄድበት የሰገን ወንዝ ፍሰቱ በሀገር ውስጥ ብቻ በመሆኑ ስራውን ለማከናወን ምቹ አጋጣሚ መሆኑም ተናግረዋል። ከ60 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚካሄደው የቅድመ አዋጭነትና የአዋጭነት ጥናት በሚቀጥሉት 18 ወራት የሚካሄድ ነው የተባለው። ጥናቱ እንደተጠናቀቀም ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና የግል አልሚዎች ተረክበው ወደ ግንባታ እንዲገቡ እንደሚደረግ ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። ግንባታውን የሚያካሂደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽንና ቁጥጥር ስራዎች ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ተሾመ ሲዳላ ግድቡ በሚያርፍበት አከባቢ የሚኖረውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ላይ ጥናት እንደሚደረግ ተናግረዋል። በውሉ መሰረት የባለሙያዎች ስብጥርና ልምድ በመጠቀም የቅድመ አዋጭነትና የአዋጭነት ጥናቱን በ18 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በፊርማው ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የደቡብ ክልል ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ በበኩላቸው በክልሉ የሚነሱ የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሰጠው ዕድል አመስግነዋል። በዛሬው ዕለት የተፈረመው የሃይል ማመንጫ ግንባታ ስራው አካባቢው በስምጥ ሸለቆ ያለና ውሃ አጠር በመሆኑ በተደጋጋሚ የሚከሰትን ድርቅ ከመከላከል አንጻር ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው ነው ያሉት። የጥናት ስራው በተገቢውና በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በክልሉ የሚገኙ ባለሙያዎችና ባለ ድርሻ አካላትን በማቀናጀትና ማህበረሰቡን በማሳተፍ ጠንካራ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
አገራት በሳይበር ምህዳሩ ዘላቂ የሆነ ጥቅም ለማግኘት ትውልድ ተሻጋሪ የአቅም ግንባታ ስራ መስራት ይገባቸዋል - አቶ ሰለሞን ሶካ
Jun 1, 2023 95
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፦ አገራት በሳይበር ምህዳሩ ዘላቂ የሆነ ጥቅም ለማግኘት ትውልድ ተሻጋሪ የአቅም ግንባታ ስራ መስራት እንደሚገባቸው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። በሞሮኮ እየተካሄደ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን የያዘ ሲሆን "የሳይበር ደህንነት አቅም ግንባታ ስራ ለሙያዊ ልህቀትና ለኢኮኖሚ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት ተደርጓል። በአውደ ርዕዩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በትውልድ መካከል የሚፈጠሩ የእውቀት ክፍተቶችን ለመሙላት ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል። እንደ ኢመደአ ያሉ የሳይበር ምህዳር ላይ የተሰማሩ ተቋማት የሰው ኃይል አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ድጋፍ መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢመደአ ብቁ እና ወሳኔ ሰጪ አመራር ለማፍራት የሚያስችሉ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል። የሰው ኃይልን ከትምህርት የተመረቁ ብቻ ይዞ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና ቀጣይነት ያለውን የበቃ የሰው ሃይል ልማት ማስቀጠል ስለማይቻል ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች መልምሎ እና እውቀታቸውን ለማጎልበት መስራት እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት። በተያያዘም የሳይበር ጥቃት ከዓለማችን ቀዳሚ ስጋቶች አንዱ መሆኑንና ምህዳሩ ፍጹም ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች እንደሆነ ተናግረዋል። ከዚህ አንጻር አገራት በሳይበር ምህዳሩ ላይ በሚሰሩ ስራዎች ላይ በትብብርና በቅንጅት ሊሰሩበት እንደሚገባ መግለጻቸውን ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ ነገ ይጠናቀቃል።
'ጂ አይ ቴክስ አፍሪካ' በሞሮኮ ማራካሽ ከተማ መካሄድ ጀመረ
Jun 1, 2023 106
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- 'ጂ አይ ቴክስ አፍሪካ' 2023 /GITEX Africa 2023/ በሞሮኮ ማራካሽ ከተማ መካሔድ ጀምሯል። በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው 'ጂ አይ ቴክስ አፍሪካ' ላይ ኢትዮጵያ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶክተር) በሚመሩትና የሚኒስቴሩ የስራ ኃላፊዎችና በውድድር የተመረጡ የቴክኖሎጂ ጀማሪ ካምፓኒዎች (ስታርታፖች) በተካተቱበት የልዑካን ቡድን እየተሳተፈች ትገኛለች። በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከናወነ የሚገኘው 'ጂ አይ ቴክስ አፍሪካ' ተቀዳሚ ዓላማ በአህጉሯ እየተካሄደ የሚገኘውን የቴክኖሎጂ አብዮት ለተቀረው ዓለም ማስተዋወቅ ነው። ባለፋት ሁለት አመታት መሠረታቸውን አፍሪካ ያደረጉ በርካታ ጀማሪ የቴክኖሎጂ ፈጣሪ ካምፓኒዎች በዓለምአቀፉ መድረክ በስፋት መታየት እና ተጽዕኖ መፍጠር ጀምረዋል። ዶክተር በለጠ ኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞን እውን ለማድረግ ባለፉት ሶስት ዓመታት ያከናወነቻቸውን ተግባራት፣ እያደረገች ያለውን ጥረቶች፣ የተገኙ ውጤቶችን እና ያጋጠሙ ችግሮችን ማብራሪያ መስጠታቸውን ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ሚኒስትሩ በቀጣይ እንደ አፍሪካ በቅንጅት መካሄድ አለባቸው ባሏቸው ጉዳዮች ላይም ሃሳባቸውን ለመድረኩ አጋርተዋል። አክለውም ኢትዮጵያ በርካታ ለስራ ዝግጁ የሆኑ ወጣቶች፣ ቴክኖሎጂን ትኩረት ያደረጉ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የዲጂታል ዘርፍ ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ የህግ ማዕቀፍና ለስራ ዝግጁ የሆነ የአይ ሲቲ ፓርክ እንዳላትም አሳውቀዋል። ሚኒስትሩ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስ ተጠቃሚ እንዲሆኑና እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል ።
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቴክኖሎጂ የታገዘ የመማር ማስተማር ሥርዓትን በመዘርጋት ተወዳዳሪ ለመሆን ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር ትብብሩን አጠናክሮ ይቀጥላል - ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና
May 31, 2023 93
አዲስ አበባ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ) አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቴክኖሎጂ የታገዘ የመማር ማስተማር ሥርዓትን በመዘርጋት ተወዳዳሪ ለመሆን ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር ትብብሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና ተናገሩ። ኢትዮ-ቴሌኮም በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር የቴሌ-ብር አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎች የዲጂታል አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ሥምምነት አድርጓል። ሥምምነቱን የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና ፈርመውታል። ሥምምነቱ በዩኒቨርስቲው የሚገኙ 18 ካምፓሶች ከፍተኛ ፍጥነት ባለው ኢንተርኔት ማገናኘት፣ ስማርት ክፍሎችን መገንባትና የተለያዩ የዲጂታል አገልግሎቶችን ማቅረብ ይገኝበታል። የብሮድ ባንድ ኢንተርኔት አቅርቦት፣ የእውቀት ሽግግርና የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ የምርምርና ፈጠራ ሥራዎችን የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችንና የመሰረተ-ልማት ግንባታዎችን ማከናወንም እንዲሁ። ያም ብቻ ሳይሆን ሥምምነቱ ተማሪዎች የትምህርት ክፍያቸውን በቀላሉ በቴሌ-ብር በኩል መፈጸም የሚያስችል መሆኑም ነው የተጠቀሰው። በተለይም የቴሌ-ብር አገልግሎት ነባርና አዲስ ተመዝጋቢ ተማሪዎች የምዝገባ፣ የፈተና የማመልከቻ፣ የሰነድ ማረጋገጫና ሌሎች ክፍያዎችን ካሉበት ቦታ ሆነው መፈጸም ያስችላቸዋል ተብሏል። የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ኩባንያው ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሁሉም ረገድ እየሰራ ነው። በተለይም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእውቀት ማመንጫና የምርምር ተቋም እንደመሆኑ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚ ማዕከል እንዲሆን ቴሌኮሙ ቀጣይነት ያለው ሥራ በጋራ ይሰራል ብለዋል። በመሆኑም ዩንቨርሲቲው በዋና ተልዕኮው ላይ ትኩረት በማድረግ ሲሰራ ቴሌኮሙ ደግሞ በዲጂታል ግንባታ ከዩንቨርሲቲው ጎን ይሆናል ነው ያሉት። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና በበኩላቸው የአገራት ብልጽግናና እድገት የሚደገፈው በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ዩንቨርሲቲው ብቃት ያለው የተማረ የሰው ኃይልን ለማፍራት በቴክኖሎጂ የታገዘ ጥናትና ምርምር፣ እንዲሁም የመማር ማስተማር ሥርዓትን በመዘርጋት ተወዳዳሪ ለመሆን ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር ያለውን ግንኙነት አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም ከኩባንያው ጋር የስማርት ክፍሎችን እውን ያደረገ ሲሆን፤ የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚነቱን እያሰፋ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የትምህርት ተቋም ለመሆን ይሰራል ብለዋል። ከዚህ ቀደም ሁለቱ ተቋማት በድህረ ምረቃ የትምህርት መርሃ ግብር በቴሌኮሙኒኬሽን ኔትዎርክ ኢንጂነሪንግና የቴሌኮሚዩኒኬሽን ኢንፎርሜሽን ሲስተም የሙያ መስኮች የጋራ ሥርዓተ-ትምህርት ቀርጸው ወደ ሥራ ገብተዋል። ሁለቱ ተቋማት ያላቸውን አጋርነት ይበልጥ በማጠናከር በአገሪቱ የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሳለጥ በጋራ እንደሚሰሩ ተገልጿል።
ኢትዮ ቴሌኮም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር የዲጂታል አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ
May 31, 2023 70
አዲስ አበባ ግንቦት 23 /2015(ኢዜአ):-ኢትዮ ቴሌኮም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር የዲጂታል አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ስምምነት ዛሬ ተፈራርሟል። ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና ናቸው። ስምምነቱ ኢትዮ ቴሌኮም በዩኒቨርሲቲው የቴሌ ብር አገልግሎትን ጨምሮ የ’ኮኔክቲቪቲ’ እና ዲጂታል አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው ነው። አገልግሎቱ 18 ካምፓሶች ከፍተኛ ፍጥነት ባለው ኢንተርኔት ማገናኘት፣ ስማርት ክፍሎችን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርና የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ የምርምርና ፈጠራ ስራዎችን የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችንና የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ለማከናወን እንዲሁም ተማሪዎች የትምህርት ክፍያቸውን በቀላሉ በቴሌ ብር በኩል መፈጸም የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ ኩባንያው ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየሰራ ነው ብለዋል። በተለይም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእውቀት ሽግግር የሚካሄድበት ስፍራ በመሆኑ በቴክኖሎጂ እና ‘ኮኔክቲቪቲ’ በማገዝ በሚጠበቅበት ልክ ውጤታማ እንዲሆን እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና በበኩላቸው፣ የተማረ የሰው ኃይል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲው ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ያለውን ግንኙነት አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም ከኩባንያው ጋር የስማርት ክፍሎችን እውን እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚነቱን በማስፋት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የትምህርት ተቋም ለመሆን በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል።
ኢትዮጵያን ወክለው በ7ኛው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ፍጻሜ ውድድር የተሳተፉ ተማሪዎች ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ
May 29, 2023 136
አዲስ አበባ ግንቦት 21/2015(ኢዜአ)፦ በ7ኛው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ፍጻሜ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉት ተማሪዎች ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። ውድደሩ ከግንቦት 16 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2015 በቻይና ሼንዘን ከተማ የተካሄደ ሲሆን በውድድሩ ከ36 አገሮች የተውጣጡ 146 ቡድኖች ተሳትፈዋል፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ተማሪዎቹ እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን በመሆን በፕራክቲካል ትራክ (ዳታኮም፣ሴኪዩሪቲ፣ገመድ አልባ የኮምፒዩተር ኔትወርክ ፣ ቢግ ዳታ፣ ስቶሬጅ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ‘OpenEuler’ እና ‘OpenGauss’ የተሰኙ የመረጃ ቋትና የአሰራር ስርዓቶችን ያካትታል) ሁለት ቡድን እና አንድ ቡድን በኢኖቬሽን ትራክ ላይ ተሳትፈዋል። በኢኖቬሽን ትራክ የተወዳደሩት ተማሪዎች “የግዕዝ ፊደላት ክላሲፋየር” የተሰኘ የፈጠራ ስራ መወዳደሪያ ይዘው መቅረባቸውን የትምህርት ሚኒስቴር በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መረጃ አመልክቷል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ውጤቱ ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች በሌሎችም ዘርፎች በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉ ያሳየ ነው ብለዋል። የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርትን ጥራት ለማረጋገጥ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆነው አገርን የሚያስጠሩ ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁዋዌ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሊዩ ጂፋን ተማሪዎቹ ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን ገልጸው ድርጅቱ የአይሲቲ ዘርፉን ለማጠናከርና ተተኪዎችን ለማፍራት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አመልክተዋል። ተማሪዎቹ በውጤታቸው መደሰታቸውንና ውድድሩ የሁዋዌን ዋና መስሪያ ቤት ከመጎብኘት አንስቶ ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ያገኙበት መሆኑን ተናግረዋል። ተማሪዎቹ በዓለም አቀፍ ውድድሩ ላይ የተሳተፉት የአገር ውስጥ ማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍና በአገር አቀፍና አህጉራዊ ውድድሮች በማሸነፋቸው እንደሆነ ተገልጿል። በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ተማሪዎች ከጎንደር፣ ዋቸሞ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲዎች የተገኙ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ስማርት የመማሪያ ክፍል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስራ አስጀመረ
May 26, 2023 156
አዲስ አበባ ግንቦት 18/2015 (ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ስማርት የመማሪያ ክፍል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማቋቋም ዛሬ በይፋ ስራ አስጀምሯል። ኢትዮ-ቴሌኮም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ስማርት የመማሪያ ክፍሎችን ለማስረጽ የሚያስችለውን ተግባር ለማከናወን ከትምህርት ሚኒስቴርና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። በስምምነቱ መሰረት ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራት ኪሎ ካምፓስ ያስገነባው የመማሪያ ክፍል ስራ ጀምሯል። በኩባንያው እውን የሆነው የስማርት መማሪያ ክፍሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸው መሆኑ ተገልጿል። ይህም የመማር ማስተማሩን ሂደት ከተለመደው አካሄድ በተሻለ ቀላል እንደሚያደርገው የተጠቆመ ሲሆን በዚህም ተማሪዎች ከልማዳዊ ትምህርት በማለፍ በተግባራዊ ተሞክሮ የበለጸገና የተሻለ የትምህርት ተሞክሮ እንዲኖራቸው ያስችላቸዋል ተብሏል። የስማርት ክፍሉ መምህራን በቀላሉ ማስተማር እንዲችሉ እንዲሁም የንድፈ ሃሳብ ትምርቶችን በቴክኖሎጂ ቤተ-ሙከራ እንዲደገፉ ያስችለዋል ነው የተባለው። ይህም የተማሪዎችን ሁኔታ ለመከታተል ፣የምዘና ፈተናዎችን ለማረምና ውጤቶችን ለማሳወቅ እንደሚያስችል ተመላክቷል።
ሶስተኛው አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የመዝጊያ መርሐ-ግብር በመካሄድ ላይ ነው
May 26, 2023 159
አዲስ አበባ ግንቦት 18 ቀን 2015 (ኢዜአ) ፡- "ክህሎት ለተወዳዳሪነት" በሚል መሪ ሀሳብ ላለፋት 5 ቀናት ሲካሄድ የቆየው ሶስተኛው አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የመዝጊያ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው። በስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት በተካሄደው የውድድር መድረኩ 267 የሚሆኑ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች በተለያዩ ዘርፎች የክህሎት ውድድር አካሂደዋል፡፡ በውድድሩም በቴክኒክና ሙያ ተቋማት አሰልጣኞች፣ ሰልጣኞች እና ኢንተርፕራይዞች የተሰሩ ከ103 በላይ የተለያዩ የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ቀርበው ተጎብኝተዋል፡፡ ከ10 ያላነሱ የዘርፉ ተግዳሮቶች ላይ ያተኮሩ ተግባራዊ የጥናትና ምርምር ሥራዎች እና የፓናል ውይይቶችም ተካሂደዋል፡፡ በተጨማሪም በሞዴል ኢንተርፕራይዞች የተመረቱ ሀገር በቀል ምርቶችም በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች ቀርበው ግብይት ተከናውኗል፡፡ የተሻለ ውጤት ላመጡ ተወዳዳሪዎች የሽልማትና የእውቅና መርሐግብር እንደሚካሄድም ተገልጿል። በመዝጊያ ስነ-ስርዓቱ ላይ የስራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
ስምንተኛው ሃገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ነገ በአሶሳ ይጀመራል
May 25, 2023 194
አሶሳ ግንቦት 17 /2015 (ኢዜአ) ፡- ስምንተኛው ዓመታዊ ሃገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ነገ እንደሚጀመር የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ። ኮንፍረንሱ “የምርምርና ዩኒቨርሲቲ ትስስር ለዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ሀሳብ እንደሚካሄድ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር አብዱልሙሃሰን ሃሰን ዛሬ ለኢዜአ ገልጸዋል። ዓላማው ተመራማሪዎች ምርምራቸውን በማቀናጀት ለሃገር ዘላቂ ልማት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ለማጠናከር መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት የሚካሄደው ኮንፍረንሱ እስከ ግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም. እንደሚቆይ ጠቁመው፤ ከአዲስ አበባ፣ ጎንደር ፣ሃሮማያና ጅማን ጨምሮ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ይሳተፋሉ ብለዋል፡፡ በዚህ ሀገር አቀፍ ኮንፍረንስ 25 ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው የሚጠበቅ መሆኑን ዶክተር አብዱልሙሃሰን አስታውቀዋል። ጥናታዊ ጽሁፎቹ በኢንጂነሪንግና ተክኖሎጂ፣ በተፈጥሮ፣ በጂኦሎጂ፣፣ በግብርና፣ በቢዝነስ፣ በኢኮኖሚክስ፣ በማህበራዊ ሳይንስና ሌሎችም ዘርፎች ላይ እንደሚያተኩሩ ጠቁመዋል፡፡ ሰባተኛው ሃገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስም በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት መካሄዱንና ይህም ሳይንሳዊ እውቀቶች በመለዋወጥ ተቀናጅተው መስራት ያስቻለ ግንዛቤ ተገኝቶበት እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በስምንተኛው ኮንፍረንስም የሚቀርቡ ጽሁፎች ዩኒቨርሲቲዎች የትምህርትና የልህቀት ማዕከላትን የመደገፍ ሃገራዊ የትኩረት አቅጣጫን በማገዝ ምርምሮች ወደ ተግባር የሚቀየሩበትን ተሞክሮ የሚያሳድጉ መግባባቶች ይደረስበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስረድተዋል፡፡
ማዕከሉ በሽታን በመቋቋም ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የዝንጅብል ዝርያዎች ለማውጣት ምርምር እያካሄደ መሆኑን አስታወቀ
May 24, 2023 187
ጎንደር፤ ግንቦት 16 ቀን 2015 (ኢዜአ) ፡- የጎንደር ግብርና ምርምር ማዕከል በሽታን በመቋቋም ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የዝንጅብል ዝርያዎችን ለማውጣት በ36 ዝርያዎች ላይ ምርምር እያካሄደ መሆኑን አስታወቀ፡፡ የምርምሩ ስራ በጭልጋ ወረዳ የተከሰተውን የዝንጅብል በሽታ ለመከላከል ዝርያዎችን በአዲስ ለመተካት መሆኑ ተገልጿል። የማዕከሉ አስተባባሪ አቶ ምንተስኖት ወርቁ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በጭልጋ ወረዳ በተከሰተው በሽታ በሰባት ቀበሌዎች በዝንጅብል ይለማ የነበረ 300 ሄክታር መሬት ላለፉት አስር ዓመታት ከዝንጅብል ምርት ውጪ ሆኗል።፡ ለበሽታው መከሰተም የአካባቢው አርሶ አደሮች ጥራትና እውቅና የሌላቸው የዝንጅብል ዝርያዎችን በመጠቀማቸው የመጣ ችግር መሆኑን ባካሄዱት ምርምር ማረጋገጣቸውን አስረድተዋል፡፡ ይሄን ችግር ለመፍታት በሽታ የመቋቋም አቅም ያላቸውንና ምርታማ የሆኑ የዝንጅብል ዝርያዎችን በምርምር በመለየት ባለፉት አራት ዓመታት የዝርያ ማሻሻል ስራ ሲያካሂድ መቆየቱን ገልጸዋል። ለዚህም ማዕከሉ ለአካባቢው ስነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑትን 36 የዝንጅብል ዝርያዎች ላይ ምርምር በማካሄድ በሽታን በመቋቋም ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ 16ቱን በመለየት በቤተ ሙከራ ተጨማሪ ምርምር እያካሄደ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ከአማራ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የቲሹ ካልቸር ምርምር ማዕከል ጋር በመተባበር ከበሽታ የጸዱ ሁለት ዝርያዎችን ለይቶ በማሳደግ ላይ እንደሚገኝ አስተባባሪው ጠቅሰዋል፡፡ በቀጣይ በሰርቶ ማሳያና በገበሬ ማሳ ላይ በማላመድና በማስተዋወቅ አርሶ አደሩ ዳግም ወደ ዝንጅብል ማምረት እንዲመለስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በጭልጋ ወረዳ በዝንጅብል ልማት የተሰማሩ ከአንድ ሺህ በላይ አርሶአደሮች በዓመት ከ84ሺህ ኩንታል በላይ ዝንጅብል አምርተው ለገበያ ያቀርቡ እንደነበር የተናገሩት የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት የሰብል ልማት አስተባባሪ ወይዘሮ ጸሃይ ዘሩ ናቸው፡፡ አሁን ላይ ግን በዝንጅብል ይለማ የነበረው ከ300 ሄክታር በላይ መሬት ከምርት ውጭ በመሆኑ አርሶ አደሮቹ ከፍተኛ ገቢ ከሚያገኙበት የዝንንጅብል ምርት በመውጣታቸው ገቢያቸው መቀነሱን ገልጸዋል፡፡ የጎንደር የግብርና ምርምር ማዕከል ችግሩን በመፍታት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በወረዳው የከንበራ ቀበሌ አርሶአደር ሲሳይ መኳንንት በሰጡት አስተያየት፤ በተከሰተው በሽታ በግማሽ ሄክታር መሬት ላይ አለማ የነበረውን የዝንጅብል ምርት በማጥፋቱ ተስፋ ቆርጩ ከዝንጅብል ምርት ወጥቻለሁ ብለዋል፡፡ አሁን ላይ ማዕከሉ በሚያደርገው ምርምር በሽታን የሚቋቋም አዲስ የዝንጅብል ዝርያ ከቀረበላቸው ከፍተኛ ገቢ ወደ ሚያስገኘው የዝንጅብል ልማት ዳግም እንደሚመለሱ ገልጸዋል፡፡ በዚሁ ወረዳ የቤዛዋ ቀበሌ አርሶ አደር በላይ መንግስቱ ፤ በዝንጅብል ከሚያለሙት ሩብ ሄክታር መሬት 70 ኩንታል ያገኙ እንደነበር አስታውሰው፤ በተከሰተው በሽታ ምክንያት ማምረት እንዳቆሙ ተናግረዋል፡፡ የምርምር ማዕከሉ አዲስ ዝርያ እንዲያቀርብልን በተደጋጋሚ እያሳሳብን እንገኛለን ያሉት አርሶአደሩ፤ ዝንጅብል አምርተው በመሸጥ በሚያገኙት ገቢ ኑሮቸውን ማሻሻል ችለው እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡ የዝንጅብል ምርት ለምግብ ማጣፈጫ ለመድሃኒት መቀመሚያና ለመዋቢያ ምርቶች በግብአትነት በስፋት የሚውል የግብርና ምርት መሆኑ ተመልክቷል።
የግብርናን ጨምሮ ሌሎች ልዩ ልዩ ምርቶች እንደ አዕምሯዊ ንብረት የሚጠበቁበትን ስርዓት መፍጠር ያስችላል የተባለ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ
May 24, 2023 162
አዲስ አበባ ግንቦት 16/2015(ኢዜአ)፡-የግብርናን ጨምሮ ሌሎች ልዩ ልዩ ምርቶች እንደ አዕምሯዊ ንብረት የሚጠበቁበትን የሕግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት የሚያስችል ፕሮጀክት ዛሬ ይፋ ሆኗል። ለሶስት ዓመት የሚተገበረው ፕሮጀክት ወጪ በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ እንደሚሸፈን ተገልጿል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር በለጠ ሞላ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ያሏትን ታዋቂ የግብርና ምርቶች በአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። ከሕግ ማዕቀፉም ጎን ለጎን ከኢትዮጵያ የግብርና ምርቶች አንዱና ዋንኛ የሆነውን የቡና ምርት ላይ የተለየ ትኩረት መሰጠቱን አድንቀዋል። የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የማህበረሰብ ዕውቀት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ወርቁ በበኩላቸው የሕግ ማዕቀፉን የያዘው ፕሮጀክት ኢትዮጵያ ውስጥ በቦታ ስም ለሚገለጹ ምርቶች አዕምሯዊ መብት ጥበቃ የሚያደርግ ነው ብለዋል። ይህም ምርቶችን የሚያመርቱ አካላትን ተወዳዳሪ ለማድረግ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ መልከዐ ምድርን የሚያመላክት የሕግ ማዕቀፍና የአሰራር ስርዓት እንዲዘረጋ የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል። በመሆኑም አዋጅና ደንብ በማዘጋጀት የንግድ ምልክቶችን ባለቤትነት ለማስጠበቅ ከተሞከሩ ሂደቶች በተጨማሪ በቦታ ጥራታቸው የሚጠቀሱ ልዩ ልዩ ምርቶችን እንደ አዕምሯዊ ንብረት የሚጠበቁበትን ስርዓት ለመፍጠር ፕሮጀክቱ ወሳኝ ጠቃሜታ አለው ነው ያሉት አቶ ታደሰ። ኢትዮጵያ ውስጥ የግብርና ምርቶች ዋንኛ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ በመሆናቸው ፕሮጀክቱ የግብርና ምርትን የሚያመርቱ አምራቾች የግብይት ሰንሰለት ውስጥ በመግባት ፍትሐዊ ተወዳዳሪ እንዲሆኑና ከምርቶች የሚገኘውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በአግባቡ እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል። በተጨማሪም በዘርፉ ያሉ ክፍተቶችን በማየትም የአቅም ግንባታ ስራዎችን ለማከናወንና የምርቶች መጭበርበር ተከስቶ ተጠቃሚዎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመከላከል እንደሚያስችልም አመልክተዋል።
በባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ ልማት አርሶ አደሩን የታዳሽ ኃይል እና ተፈጥሮ ማዳበሪያ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተደረገ ነው - የኦሮሚያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ
May 23, 2023 138
አዲስ አበባ ግንቦት 15/2015(ኢዜአ)፡-በባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ ልማት አርሶ አደሩን የታዳሽ ኃይል እና ተፈጥሮ ማዳበሪያ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተደረገ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ገለጸ። በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ ሸዋ ዞን በወልመራ ወረዳ በኢትዮጵያ መንግስት እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር የተገነባ "የጋባ ሮቢ ሞዴል ባዮጋዝ መንደር" ፕሮጀክት ተመርቋል። በምርቃቱም የፌደራል፣ የክልል መንግስታት የስራ ኃላፊዎች፣ የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ጨምሮ የዞንና የወረዳ የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የኦሮሚያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር መሀመድ ዚያድ፤ በክልሉ ከፌደራልና ከለጋሽ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ ልማት የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው። የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ አቅም ያላቸው ወረዳዎች በማተኮር የአርሶ አደሩ የኃይል አማራጭ ባሻገር የአፈር ለምነትን በመመለስ ምርታማነቱን እንዲያሳደግ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። በተያዘው በጀት ዓመት ወደ 10 ሺህ የሚጠጋ የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ ልማት መከናወኑን ገልጸው፤ በቀጣይም ይህ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ ባዮ ጋዝ ፕሮግራም ኃላፊ አቶ ተመስገን ተፈራ፤ የባዮ ጋዝ ልማት በተለያዩ ክልሎች ለኃይል አማራጭ እና ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስችሏል ብለዋል። 10 ዓመታትን ባስቆጠረው የባዮ ጋዝ ልማት ፕሮግራም ትግበራ አርሶ አደሮችን በኤሌክትሪክ፣ የተፈጥሮ ማዳበሪያ፣ በስራ እድል ፈጠራ እና በአካባቢ ጥበቃ ስራ ተጠቃሚ መሆናቸውንም ነው ያነሱት። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኤሊያስ ከድር የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ አርሶ አደሩን በተፈጥሮ ማዳበሪያ በማስጠቀም በአሲዳማና ጨዋማነት የተጠቃን አፈር ለምነት እንዲመለስ አስችሏል ብለዋል። የሞዴል የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ መንደሮችን በማስፋትም አርሶ አደሩን በኃይል አማራጭ አቅርቦት እና በአፈር ለምነት ተጠቃሚ እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል። የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ እና መሰረተ ልማት ቡድን መሪዋ ሳኔ ዊሊያም ህብረቱ የአርሶ አደሮችን የኃይል አማራጭ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የቴሌኮምዩኒኬሽን ኩባንያው ኢቲሳላት በኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፍ የመሰማራት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ
May 23, 2023 129
አዲስ አበባ ግንቦት 15/2015(ኢዜአ):-የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቴሌኮምዩኒኬሽን ኩባንያ ኢቲሳላት በኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፍ የመሰማራት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ። የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከኢቲሳላት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሃተም ዶዊዳር ጋር በበይነ መረብ ተወያይተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚው ኩባንያው በኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፍ የመሰማራት እንዲሁም በዘርፉ ያሉ የኢንቨስትመንት እድሎችን ለመመልከት ከኢትዮጵያ መንግስትና የዘርፉ ተዋናዮች ጋር ለመስራት ፍላጎት እንዳለው ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች በቀጣዮቹ ሳምንታት በኢትዮጵያ ተገናኝተው ውይይታቸውን ለመቀጠል መስማማታቸውን ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቴሌኮምዩኒኬሽን ኩባንያ ኢቲሳላት የተቋቋመው እ.አ.አ በ1976 ነው። ኩባንያው በአፍሪካ፣ እስያና መካከለኛው ምስራቅ በሚገኙ 16 አገራት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን 12 ሚሊዮን የሚጠጉ ደንበኞች እንዳሉት መረጃዎች ያመለክታሉ። በኢትዮጵያ ለሶስተኛው የቴሌኮም አገልግሎት ሰጭ ተቋም ፈቃድ ለመስጠት በሰኔ 2015 ዓ.ም ጨረታ እንደሚወጣ የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከቀናት በፊት ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራ አባላት የእውቀት፣ ክህሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው ተመለከተ
May 22, 2023 196
ጅማ ግንቦት 14/2015 ( ኢዜአ) ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ አባላት የእውቀት፣ ክህሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት አስገነዘበ። በሀገር ውስጥ በርካታ ተቋማት የቴክኖሎጂና የአቅም ግንባታ ስልጠና ፍላጎት ያላቸው ቢሆንም በውጭ የሚኖረው ዳያስፖራ ማሕበረሰብ የሚያደርገው ድጋፍ የተቀናጀ አለመሆኑ ተመልክቷል። በዚሁ ጉዳይ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ከጅማ፣ ከሀዋሳ፣ ከጂግጂጋ እና ከወሎ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አንድ አመት የፈጀ የዳሰሳ ጥናት ይፋ አድርጓል። የጥናቱ አላማ የተማረው ዳያስፖራ እውቀቱን፣ ክህሎቱንና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በተቀናጀና በተደራጀ ሁኔታ ሀገሩን ማገዝ እንዲችል ያለውን መልካም አጋጣሚ መለየት ነው ተብሏል። የጥናቱ አስተባባሪና በጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር መኮንን ቦጋለ እንዳሉት በጥናቱ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ የጤና ተቋማት እና የዲያስፖራ ቢሮ ተዳሷል። የጥናትና ምርምር ትብብር፣ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች፣ የቴክኖሎጂ ማእከላት ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ የታገዙ የጤና መመርመሪያ ማእከላት ግንባታ እና በዲፕሎማሲው ዘርፍም የዳያስፖራው እገዛ እንደሚያስፈልግ በጥናቱ ተመላክቷል ብለዋል። በጥናቱ 103 የፕሮፌሽናል ዲያስፖራ ማህበራት ተወካዮች የተጠየቁ ሲሆን ሀገራቸውን የማገዝ ፍላጎት እንዳላቸው ቢገልጹም በምን እና እንዴት ማገዝ እንዳለባቸው ለይተው አላስቀመጡም ነው ያሉት። ሌላው የጥናቱ አስተባባሪ አቶ ጥበቡ ታፈሰ በበኩላቸው ከሀገር ውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊውያን በተቀናጀና በተናበበ መንገድ ሀገራቸውን ማገዝ እንዲችሉ ጥናቱ መሰራቱን ተናግረዋል። በተለይም በተለያዩ የውጭ ሀገራት ያሉ ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራዎች ያላቸውን ክህሎት ፣እውቀትና የቴክኖሎጂ በማሸጋገር በእናት ሀገራቸው እድገትና ብልፅግና ጉዞ በመሳተፍ አስተዋጽዎ እንድያደርጉ ለማስቻል ያለመ ጥናት ነው ብለዋል። አብዛኛው የዳያስፖራው ማህበረሰብ ሀገሩን በማንኛውም ሁኔታ ለማገዝ ቀናኢ መሆኑን ያነሱት አቶ ጥበቡ ይህንን ሀብት ማቀናጀትና በታቀደ አሰራር ለመተግበር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት በውጭ የሚኖሩ ዜጎች መብት የህግ ከለላ ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ገዛኸኝም እንዲሁ የዳያስፖራውን ማሕበረሰብ በማቀናጀት ለሀገሩ ተገቢውን እገዛ እንዲያደርግ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። ሀገሩን የሚወድ ዳያስፓራ በአጠቃላይ ለሀገሩ የሚያደርገው ነገር ትልቅ ትርጉም እንዳለው በመገንዘብ ለሀገራቸው እውቀትንና ቴክኖሎጂን ለማሸጋገር መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። በዘመኑ በየትኛውም ዘርፍ የቴክኖሎጂ አበርክትዎ እየጎላ በመምጣቱ በተበታተነ መንገድ ሲደረግ የነበረውን ጥረት አቀናጅቶ ለመፈጸም በትኩረት ይሰራል ብለዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው የዳሰሳ ጥናት ይፋ ማድረጊያ መድረክ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት በቀረበው ጥናት ግኝት መሰረት ተወያይተው ስለአፈጻጸሙ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሏል።
የፈጠራ ባለሙያዎች በሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሳይበገሩ ለአገር ዕድገት በውጤት ተኮር ሥራዎች ሊተጉ ይገባል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ
May 22, 2023 227
አዲስ አበባ ግንቦት 14/2015 (ኢዜአ)፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የፈጠራ ባለሙያዎች በሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በውጤት ተኮር ሥራዎች ሊተጉ እንደሚገባ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ 3ኛውን ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር መድረክ በዛሬው እለት በይፋ ከፍተዋል። የውድድር መድረኩ "ክህሎት ለተወዳዳሪነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተዘጋጀ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ አምስት ቀናት የሚካሄድ ይሆናል። በውድድሩ የፈጠራ ሥራዎች አውደ-ርዕይ፣ የፓናል ውይይትና ሌሎች ዝግጅቶች እንደሚኖሩ ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ የውድድር መድረኩ ክህሎት ያላቸው ወጣቶች ብቃታቸውን ለማሳየትና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ሁነኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። በዕለቱ በተመለከቷቸው የፈጠራ ሥራዎችም ትልቅ ተስፋ መኖሩን ጠቅሰው፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በተቋቋመ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወኑም አድንቀዋል። በኢትዮጵያ በሁሉም ኢኮኖሚ ዘርፎች የግብዓት እጥረት ስለሌለ የፈጠራ ክህሎት ያላቸውን ሰዎች ማብዛትና ግብዓቶችን አመጋግቦ በመጠቀም ሀገር መለወጥ እንደሚቻል ተናግረዋል። በመሆኑም ፈጠራ ነባር ነገሮችን በአዲስ የሚተካና የመፍጠር ክህሎት የሚጠይቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ የችግሮች የመፍትሔ ቁልፍ የሆነውን ፈጠራ ፈጥኖ መቀበል እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ በርካታ ችግሮችን በድል ለመሻገር የፈጠራ ባለሙያዎች በሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በውጤት ተኮር ሥራዎች ለአገር እድገትና ብልጽግና እውን መሆን ሊተጉ ይገባል ብለዋል። በመሆኑም የፈጠራ ባለሙያዎች የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን እንደመስፈንጠሪያ በመጠቀም ውጤት ተኮር ሥራዎች ላይ አበክረው እንዲሰሩ አሳስበዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው፤ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች ከዕድገት ምንጭነታቸው ባሻገር ለተወዳዳሪ ኢኮኖሚና ለዘላቂ ልማት ወሳኝ ድርሻ አላቸው ብለዋል። የክህሎት ውድድሩ የተዘጋጀውም በየደረጃው ባሉ የቴክኒክ ኮሌጆች ሦስት እርከን ውድድሮች አድርገው የተለዩ "የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር" ነው ብለዋል። የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን ለማዘመን ሚኒስቴሩ መጠነ-ሰፊ የለውጥ ሥራዎችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል። በቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ሥር የሚገኘው የብየዳ ማዕከል ዓለም አቀፍ ዕውቅና ማግኘቱን ያስታወሱት ሚኒስትሯ፤ የዓለም አቀፉ የክህሎት ማኅበር አባል ለመሆን ሚኒስቴሩ ጥያቄ ማቅረቡንም ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በይፋ በተከፈተው የክህሎት ውድድር የክልሎች የሥራ ኃላፊዎች፣ የሚመለከታቸው አካላትና የፈጠራ ባለሙያዎች ታድመዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ነጥብ 2 ትሪሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በዲጂታል ክፍያ ስርዓት ተላልፏል
May 22, 2023 176
አዲስ አበባ ግንቦት 14/2015(ኢዜአ):- ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ነጥብ 2 ትሪሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በዲጂታል ክፍያ ስርዓት መተላለፉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለፁ። ሚኒስትሯ የመንግሥትን የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸምን ለሚኒስትር ዴኤታዎች፣ ለምክር ቤት አባላትና ለተቋማት ኃላፊዎች ባቀረቡበት ወቅት መንግሥት አካታች ኢኮኖሚን ለመገንባት በዲጂታል ፋይናንስ ላይ በትኩረት እየሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህም በፖሊሲና በአሰራር በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰው፤ በሞባይል ገንዘብ የማስተላለፍ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ60 ሚሊዮን በላይ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል። በዚህም በዘጠኝ ወራት ውስጥ ከ1 ትሪሊዮን 220 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በዲጂታል ክፍያ መተላለፉን ጠቁመዋል። ይህም ከ2014 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው የ454 ነጥብ 31 ቢሊዮን የዲጂታል ገንዘብ ዝውውር ጋር ሲነፃፀር የ169 በመቶ እድገት ማስመዝገቡን ገልጸዋል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ኢትዮጵያን ግንባታ ላይ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል። ለአብነትም የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ሙሉ ሙሉ ወደ ቴክኖሎጂ ስርዓት መግባቱን ጠቅሰዋል። የታክስ ስርዓቱንም ወደ ኤሌክትሮኒክስ ክፍያ የማስገባት ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል። ኢኮኖሚው ማህበረሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ እንዲያደርግ ሰፊ የቴሌኮም መሠረተ ልማት በመዘርጋት የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል። የኢንተርኔት ተጠቃሚ ዜጎችን ቁጥር ለመጨመርም እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል። የኢንተርፕራይዞችን እና የተቋማት የእርስበርስና ከተገልጋዮች አኳያ የብሮድባንድ ተደራሽነትን ለማስፋት በተሠራው ሥራ የ19 በመቶ ዕድገት መመዝገቡን ጠቅሰዋል። በቀጣይ የዲጂታል ኢኮኖሚና የፋይናንስ አካታችነትን ለማረጋገጥ ወጥነት ያለው፣ የተቀናጀና ተገቢው ቁጥጥር የሚደረግበት የዲጂታል ትግበራ ሊኖር እንደሚገባ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ3ኛውን ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር መድረክ በይፋ ከፈቱ
May 22, 2023 148
አዲስ አበባ ግንቦት 14/2015(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ3ኛውን ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር መድረክ በይፋ ከፍተዋል። በስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት 'ክህሎት ለተወዳዳሪነት' በሚል መሪ ሀሳብ ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ አምስት ቀናት የሚቀጥል ነው። በውድድሩ የፈጠራ ስራዎች ዐውደ ርዕይ፣ፓናል ውይይትና ሌሎች መርሀ-ግብሮች እንደሚኖሩ ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት ውድድሩ ብቃትና ክህሎት ያላቸው ወጣቶች መብቃታቸውን ለማሳየትና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ሁነኛ ሚና ይኖረዋል። ኢትዮጵያን ለማበልፀግና ሁሉንም ዘርፍ ለማዘመን ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የግብዓት ችግር ባለመኖሩ ፈጠራና ክህሎትን ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያመላከቱት። የፈጠራ ባለሙያዎች በሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች ሳይበገሩ ፈተናዎችን እንደመስፈንጠሪያ ተጠቅመው፤ ውጤት ተኮር ስራዎች ላይ አበክረው እንዲሰሩም አሳስበዋል። ዛሬ በቀረቡ የፈጠራ ስራዎችም ትልቅ ተስፋ ሰጭ ፈጠራዎችን እንደተመለከቱ ገልፀው፣ ሚኒስቴሩ በተቋቋመ በአጭር ጊዜ ውጤታማ ስራዎች ማከናወኑን ተናግረዋል።