ቀጥታ፡
ፖለቲካ
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በእውቀት እና ክህሎት የሚመራ ሰራዊት በመገንባት ሂደት ውስጥ ገንቢ ሚና እየተወጣ ነው
Oct 9, 2025 80
አዲስ አበባ፤ መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በእውቀት እና ክህሎት የሚመራ ሰራዊት በመገንባት ሂደት ውስጥ ገንቢ ሚና እየተወጣ መሆኑን በዩኒቨርሲቲው የምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ኮሎኔል ሚኒሊክ ዋለ (ዶ/ር) ገለጹ። የአህጉሪቷን ሰላም እና ደህንነት ማስከበር የሚያስችል የሰው ሀይል እያፈራ መሆኑንም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የምርምር አስተዳደርን፣ ፈጠራንና የማኅበረሰብ ተሳትፎን ማጎልበት ላይ ያተኮረ የሁለት ቀናት አውደ ጥናት ማካሄድ ጀምሯል።   ዓላማውም ከተለያዩ ተቋማት የመጡ አመራሮች እና ሙያተኞች በምርምር፣ በፈጠራ፣ በማህበረሰብ ግልጋሎት እና በቴክኖለጂ ሽግግር ላይ ያላቸውን ተሞክሮ ለዩንቨርሲቲው እንዲያካፍሉ ማስቻል ነው። የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ኮሎኔል ሚኒሊክ ዋለ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የሰራዊቱን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ ምርምር ወሳኝ ነው። ከዚህ አኳያ ዩንቨርሲቲው በተሰጠው ተልዕኮ በእውቀት እና ክህሎት የሚመራ ሰራዊት በመገንባት ሂደት ውስጥ ገንቢ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ዩንቨርሲቲው ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ተማሪዎችን በመቀበል እያስተማረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ከዩንቨርሲቲው የወጡ ምሩቃን አገራቸውን በተለያየ የአመራር ደረጃ እያገለገሉ እንደሚገኙ ገልጸው፤ ይህም ኢትዮጵያ ከሀገራት ጋር በጋራ ለማደግ እና ደህንነትን ለማስከበር ያላትን ጽኑ አቋም የሚያሳይ መሆኑን አስታውቀዋል። እነዚህ ተግባራት የኢትዮጵያን ስም በአፍሪካ ውስጥ ከፍ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። በመከላከያ ዋር ኮሌጅ የስትራቴጂያዊ ጥናት ኢንስቲቲዩት ዲን ስራው ደማስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መከላከያ በርካታ የትምህርት እና የምርምር መሰረተ ልማቶችን የያዘ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። ስልጠናው እነዚህን ሀብቶች እንዴት በጋራ መጠቀም እንደሚቻል ግንዛቤ የሚፈጥር መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪ የምርምር ፐሮጀክቶችን በጀት እንዴት መጠቀም እና ማፈላለግ እንደሚቻል ትምህርት ያገኙበት መሆኑን ጠቁመዋል። አውደ ጥናቱ አጋዥ የሆኑ የምርምር ውጤቶችን ከማውጣት አኳያ የትኩረት አቅጣጫዎችን ያመላከተ መሆኑን በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ እና ማህበራዊ ጥናት ኮሌጅ ዲን አይችሉም ከተማ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። በተለይም በበጀት አጠቃቀም እና በፋይናንስ ምንጭ ላይ ግንዛቤ የተገኘበት መሆኑን አመልክተዋል።    
ኢትዮጵያና ቤልጄም የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብራቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ -አምባሳደር ሀደራ አበራ
Oct 9, 2025 100
አዲስ አበባ፤ መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያና ቤልጄም በሁለትዮሽና በባለብዙ ወገን ጉዳዮች ያላቸውን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ገለጹ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በቤልጄም የውጭ የጉዳይ ሚኒስቴር የውጭ ንግድና ልማት ትብብር ዋና ጸሀፊ እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ፕሬዝዳንት ቴወዶራ ገንትዚስ ከሚመራ ልዑክ ጋር በሁለቱ ሀገሮች ዙሪያ ፖለቲካዊ ምክክር አድርገዋል፡፡   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያና ቤልጄም በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ የረጅም ዘመን አጋርነት አላቸው፡፡ የኢትዮጵያና ቤልጄም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመረው እ.አ.አ በ1906 እንደነበር አስታውሰው በመጪው የፈረንጆቹ ዓመት 120ኛ ዓመታቸውን በጋራ ያከብራሉ ብለዋል፡፡ በሁለቱ ሀራት መካከል ያለውን ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር በቀጣናዊ፣ የሁለትዮሽ እና ባለብዙወገን ጉዳዮች ላይ ተቋማዊ ትብብርን የሚፈጥር የመግባቢያ ስምምነት በቅርቡ እንደሚፈራረሙም ገልጸዋል፡፡ የፖለቲካ ምክክሮች ከሁለትዮሸ ባለፈ በአፍሪካ ህብረትና በአውሮፓ ህብረት ባሉ ባለብዙ ወገን የውጭ ግንኙነቶች ላይ በትብብር መሥራት ያስችላል ብለዋል፡፡ ቤልጄም የኢትዮጵያ የልማት አጋር መሆኗን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የልማት ትብብርና የነፃ የትምህርት ዕድል ጉልህ ሚና እንዳላት ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የቤልጄም ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን ገልጸው፤ በግብርና፣ በአረንጓዴ ኃይል፣ ሎጂስቲክስ እና አምራች ዘርፍ ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ኢትዮጵያ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ የሚያሳደግ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ገቢራዊ ማድረጓን አንስተው፤ ለዚህ ጥረት መሳካት የአየር ትራንስፖርት ትስስር እንዲያድግ እናደርጋለን ብለዋል፡፡ ቤልጄም የኢትዮጵያን ቡና በከፍተኛ መጠን ከሚገዙ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን በማንሳት፤ የአውሮፓ ህብረት በመጪው ታህሳስ ወር ገቢራዊ በሚያደርገው "የአውሮፓ ህብረት ደን ጭፍጨፋ ደንብ" አጋርነቷን እንደምታሳይ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡   በቤልጄም የውጭ የጉዳይ ሚኒስቴር የወጪ ንግድና ልማት ትብብር ዋና ጸሀፊ እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ፕሬዝዳንት ቴወዶራ ገንትዚስ በበኩላቸው ሁለቱ ሀገራት ከሁለትዮሽ ባለፈ በባለብዙ ወገን ተቋማት ከሊግ ኦፍ ኔሽን ምስረታ ጀምሮ የረጅም ዘመን ግንኙነት አላቸው ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ድምጽ በዓለም አቀፍ መድረክ መደመጥ እንዳለበት በመጥቀስ፤ ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የልብ ምት መሆኗን አረጋግጠዋል፡፡ ኢትዮጵያ አስደናቂ የኢኮኖሚ ሪፎርም ማድረጓን ገልጸው፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የኢኮኖሚ ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ የቤልጄም ተመራማሪዎችና መምህራን በኢትዮጵያ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚገኙ በመጥቀስ፤ ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠው የትምህርት ዕድል ቀጣይነት ይኖረዋል ብለዋል፡፡
ሰላምን በዘላቂነት ለማስጠበቅ የምክር ቤቱ አባላት ክትትልና ድጋፋቸውን ማጠናከር አለባቸው - አፈ ጉባዔ ኢትዮጲስ አያሌው
Oct 9, 2025 84
ወልዲያ፤ መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፡- የከተማዋንና የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ የምክር ቤቱ አባላት ድጋፍና ክትትላቸውን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለባቸው የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ኢትዮጲስ አያሌው አስገነዘቡ ። የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 17ኛ አስቸኳይ ጉባዔ እየተካሄደ ነው።   በጉባዔው መድረክ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አቶ ኢትዮጲስ እንደገለጹት፤ የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት በማስቀጠል የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የምክር ቤቱ አባላት ድጋፍና ክትትላቸውን ይበልጥ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል። በተለይ ከወከላቸው ህዝብ ጋር በየጊዜው ተገናኝቶ በመወያየትና በመምከር ሕዝቡ ከመንግስት ጎን በመቆም ሰላሙን በዘላቂነት እንዲያፀና ድጋፋቸውን ማጎልበት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የወልዲያ ከተማና አካባቢው ነዋሪ ሰላምን አጥብቆ ይሻል ያሉት አፈ ጉባዔው፣ ለዚህም በየአካባቢው ሕብረተሰቡን ያሳተፈ ቅንጅታዊ ሥራ እንደሚያስፈልግ አንስተዋል። ችግርን በመቋቋም በወልዲያ ከተማ ኮሪደርን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው፤ የምክር ቤቱ አባላት የወከላቸውን ሕብረተሰብ በማስተባበር ልማቱን የማስቀጠል ሚናቸውን ይበልጥ መወጣት እንዳላባቸው አስገንዝበዋል። ሕብረተሰቡ ለሚያነሳቸው የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች አስፈጻሚ አካሉ ምላሽ በመስጠት ሕዝባዊ እርካታን ለማረጋገጥ ክትትሉና ድጋፉን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለባቸውም ገልጸዋል። እንደ ምክር ቤት አባልነት ሕዝባዊ ውክልናችንን ተጠቅመን ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ያሉት የምክር ቤቱ አባል ደግሞ አቶ ፍስሃ መንግስቴ ናቸው። ሌላው የምክር ቤት አባል አቶ አሻግሬ ሲሳይ፤ በአካባቢው የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ስኬታማ በማድረግ ከድህነት ለመውጣት የክትትልና ቁጥጥር ሥራችንን እናጠናክራለን ሲሉ ገልጸዋል። ምክር ቤቱ በነገው እለትም ቀጥሎ የሚውል ሲሆን የ2018 የበጀት ዓመት የልማትና የፋይናንስ እቅዶች ላይ በመምከር ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።  
የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዲኖሩ ለመቀበል ዝግጁ ነን
Oct 9, 2025 85
አዲስ አበባ፤ መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፦ ከወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ። የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሸተ ደምለው እና የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በሰጡት ማብራሪያ፤ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱና ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እየተደረገ ነው ብለዋል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አሸተ ከዞኑ የተፈናቀሉና ያልተመለሱ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እንደሚቀበሏቸው ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በወልቃይት ጠገዴ የሚኖሩ በርካታ የትግራይ ተወላጆች ሰላማዊ ህይወታቸውን እየመሩ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ የአማራና የትግራይ ህዝብ ለዘመናት አብረው የኖሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሰሜኑ ጦርነት በተከሰተበት ወቅት ብዙዎች በኖሩበት አካባቢ እየኖሩ መሆኑን አስታውሰው፤ በወቅቱ ተደናግጠው ከሄዱት መካከል ደግሞ ወደ ዞኑ ተመልሰው ሰላማዊ ህይወት መምራት የጀመሩ መኖራቸውን ተናግረዋል። ምክትል ዋና አስተዳዳሪው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በበኩላቸው እንደገለጹት ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው መመለስ አለባቸው። በአካባቢው ሰላም ለመፍጠር አንድን ማህበረሰብ አፈናቅለህ አንዱን ማኖር የሚቻል አይመስለኝም ብለዋል። ምክትል ዋና አስተዳዳሪው፤ የተፈናቃዮች ጉዳይ በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝ በሁሉም በኩል ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል። መንግስት ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለማድረግ በተከታታይ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውንና ጥረቶች ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የመክፈቻ ንግግርን አስመልክቶ የቀረበውን የድጋፍ ሞሽን አዳመጡ
Oct 9, 2025 146
አዲስ አበበ፤መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለቱ ምክር ቤቶች ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ የቀረበውን የድጋፍ ሞሽን አድምጧል። 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን አንደኛ መደበኛ ስብሰባው በሁለት አጀንዳዎች ላይ ውይይት አካሂዷል።   በዚህም ምክር ቤቱ በመጀመሪያ አጀንዳው በ4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ ቃለ ጉባኤን መርምሮ በማጽደቅ ስብሰባውን ጀምሯል። በመቀጠልም በአንደኛ መደበኛ ስብሰባው ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ መስከረም 26/2018 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ መደበኛ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ የቀረበን የድጋፍ ሞሽን አዳምጧል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጂጌ(ዶ/ር) የድጋፍ ሞሽኑን አቅርበዋል።   በመጨረሻም የምክር ቤቱ አባላት ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ መስከረም 26/2018 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ መደበኛ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ በቀረበው የድጋፍ ሞሽን ላይ ተወያይተዋል።
የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራትን የመከታተል እና የመደገፉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል- ምክር ቤቱ
Oct 9, 2025 115
ወላይታ ሶዶ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው ዓመት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የክትትል እና የድጋፍ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ምክር ቤት አስታወቀ። የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን መደበኛ ጉባኤውን በነገው ዕለት በአርባ ምንጭ ከተማ ያካሄዳል። የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እንደገለጹት ምክር ቤቱ በክልሉ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የሚከናወኑ ተግባራት እንዲጠናከሩ እየሰራ ነው ። በየደረጃው የህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲኖራቸውና እየታዩ ያሉ ለውጦች እንዲጠናከሩ ምክር ቤቱ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ጉባኤው በህዝብ ዘንድ የሚነሱ ቀሪ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመመለስ የሚያግዙ አቅጣጫዎች የሚቀመጡበት እንደሆነም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
Oct 9, 2025 156
አዲስ አበባ፤ መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ እና የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ስምምነቱን በቤልጂየም ብራሰልስ መፈራረማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ስምምነቱ በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት መካከል ባለው የረጅም ጊዜ አጋርነት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነም ተገልጿል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ከስምምነቱ በፊት ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ የጋራ ስትራቴጂካዊ ራዕይን ለማሳካትና የኢትዮጵያና የአውሮፓ ህብረት አጋርነት በማይበገር ሁኔታ መገንባት የሚያስችል ጊዜውን የጠበቀ ስምምነት መሆኑን ገልጸዋል። የትብብር ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑም አክለዋል። ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል።
ኢትዮጵያ የዘመናት ችግሮቿን ተሻግራ ወሳኝ ውጤቶች ያስመዘገበችበት የታሪክ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች 
Oct 8, 2025 275
አዲስ አበባ፤ መስከረም 28/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዘመናት ችግሮቿን ተሻግራ ወሳኝ ውጤቶች ያስመዘገበችበት የታሪክ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር ) ገለጹ። የኢኮኖሚ ብልፅግና ክላስተር የ2017 በጀት ዓመት የፖለቲካ እና አደረጃጀት ስራዎች አፈጻጸም የወረዳዎች እውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው ፡፡   የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የፌዴራል ተቋማት አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ቤልጅጌ (ዶ/ር ) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ 2018 በጀት ዓመት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሰረት የተጣለበት ነው፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የተበሰረበት ወቅት መሆኑን አውስተዋል። ኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ሃብቷን አውጥታ ለመጠቀም የሚያስችሏትን ግዙፍ ፕሮጀክቶች ይፋ ማድረጓን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ አብራርተዋል። ምክትል ሰብሳቢው ተስፋዬ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚያስችል መሰረት እየተጣለ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በብልፅግና ፓርቲ መሪነትና በለውጡ መንግሥት አስተባባሪነት የዘመናት ችግሮቿን ተሻግራ ወሳኝ ውጤቶችን ያስመዘገበችበት የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝም ተናግረዋል። ብልፅግናን ለማረጋገጥ በሚደረገው እንቅስቃሴ የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን ለማለፍ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ጠቁመው፤ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እልባት እንዲያገኙ የሚጠበቅብንን ድርሻ መወጣት አለብን ብለዋል፡፡ ከአገልግሎት አሰጣጥ አኳያም ከህዝቡ የሚነሱ ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ብልፅግና ፓርቲ የዛሬ ብቻ ሳይሆን ዘመናት የሚሻገር ሀሳብና የሀሳብ ግልጽነት ያለው ነው ያሉት ምክትል ሰብሳቢው ተስፋዬ (ዶ/ር)፤ በፓርቲው እሴቶች፣ ፍልስፍናዎች፣ ሰነዶች ዙሪያ የጠራ የአመለካከት ግልጽነት መፍጠር እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ የብልፅግና ፓርቲ ፍልስፍናዎችን በተመለከተ አራት መጽሐፎች መዘጋጀታቸውን ገልጸው፤ ዋናው መቆሚያችን መደመር ነው ብለዋል፡፡ የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የኢኮኖሚ ክላስተር ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት ለመሆን ያስቀመጠችው ግብ በትክክለኛ መስመር ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡   የተፈጥሮ ጋዝ፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረጉ ፕሮጀክቶች ለዚህ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ እና ከተፈጥሮ ጋዝ ምርት የሚገኘው ሀይል የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ መሰረት በማስፋት የዜጎችን ኑሮ የሚያሻሽል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ የመንፈስ ልዕልናን የሚየጎናጽፉ፣ የጀመርነውን መጨረስ ካለምነው መድረስ እንደምንችል የሚያሳዩ የኢትዮጵያን ብልፅግና አይቀሬነት የሚያረጋገጡ ናቸው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ያስቀመጥነውን ግብ ለማሳካት በትክክለኛ መንገድ ላይ መሆናችንን ማሳያዎች ናቸው ብለዋል የኢኮኖሚና ክላስተር ሰብሳቢው አቶ መላኩ፡፡ ብልፅግና የተከታታይ ጥረቶችና ለውጦች ውጤት መሆኑን ገልጸው፤ ለተሻለ ስኬት ከዚህ በላይ መትጋት፣ ጅምሮችን መጨረስና አዳዲሶችን መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡ ከድህነት አዙሪት በመውጣት ራዕያችንን ዕውን ለማድረግ የፓርቲው አመራርና አባላት በፈጠራና በፍጥነት በእምርታ መስራት አለብን ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የእውቅና መርሃ ግብሩ በወረዳዎች መካከል በአፈፃፀም ዙሪያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግና የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ትልቅ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል፡፡
በድሬዳዋ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ  እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች ስራዎች መጠናከር አለባቸው- ቋሚ ኮሚቴው   
Oct 8, 2025 119
ድሬዳዋ ፤ መስከረም 28/2018 (ኢዜአ)፦በድሬዳዋ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመፍታት እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የከተማ፣ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ። የከተማ፣ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ዛሬ በድሬዳዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሠረተ ልማቶች እና የአገልግሎት መስጫ ተቋማትን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።   የኮሚቴው አባላት የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና፣ የደረቅ ወደብና ተርሚናል፣ የድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ አለም አቀፍ ስታዲዮም፣ የኮንቬንሽን ማዕከል እና የእመርታ ቤተ-መፅሐፍት በመጎብኘት ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አካሄደዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መሐመድ አብዶ እንዳሉት በድሬዳዋ እየተገነቡ የሚገኙ መሠረተ ልማቶች የነዋሪውን የልማትና የአገልግሎት ጥያቄዎች በፍጥነትና በጥራት እንዲመለሱ የሚያግዙ ናቸው።   የመሠረተ ልማቶቹ መገንባት ድሬዳዋን በኢንዱስትሪ፣ የንግድና የኮንፈረንስ ቱሪዝም ዘርፎች ተመራጭ ያደርጋታል ብለዋል። በተለይ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት የጀመረው መሶብ ድሬ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንቅስቃሴ አበረታችና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑን በመግለፅ። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ እሸቱ ተመስገን (ዶ/ር) በበኩላቸው በአስተዳደሩ ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ፣ ህዝብንና ድርጅቶችን አስተባብሮ የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች በአርዓያነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።   እነዚህን አበረታች ስራዎች በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል ሁሉም የአስተዳደሩ አመራሮች በትብብር መስራት አለባቸው ብለዋል። የቋሚ ኮሚቴው አባላቱ አቶ ፍቃዱ ጋሻው እና ወይዘሮ ታለፍ ፍትህአወቀ፣ በአመራሩ የተናበበ ቅንጅት የከተማ አገልግሎቶችን ለማዘመንና መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት የተጀመረው ጥረት በላቀ ደረጃ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህና ቋሚ ኮሚቴው በድሬዳዋ ተገኝቶ ያደረገው የመስክ ግምገማ በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት የሚያነቃቃ መሆኑን ገልፀዋል።   በድሬዳዋ የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ስራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅም ርብርቡ ይቀጥላል ብለዋል።
የኢትዮጵያን ብልፅግና እውን ማድረግ የሚያስችል መሰረት እየተጣለ ነው
Oct 8, 2025 151
አዲስ አበባ፤ መስከረም 28/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብልፅግና እውን ማድረግ የሚያስችል መሰረት እየተጣለ ነው ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ቤልጂጌ(ዶ/ር) ገለጹ። የኢኮኖሚ ብልፅግና ክላስተር የ2017 በጀት ዓመት የፖለቲካ እና አደረጃጀት ስራዎች አፈጻጸም የወረዳዎች እውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡   የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የፌዴራል ተቋማት አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የ 2018 በጀት ዓመት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሰረት የተጣለበት ነው፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተበሰረበት መሆኑን አውስተዋል። ኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ሃብቷን አውጥታ መጠቀም የሚያስችሏትን ግዙፍ ፕሮጀክቶች ይፋ ማድረጓን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ አብራርተዋል። ምክትል ሰብሳቢው ተስፋዬ(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያን ብልፅግና ማረጋገጥ የሚያስችል መሰረት እየተጣለ ነው ብለዋል፡፡ ብልፅግናን እውን ለማድረግ በሚደረገው እንቅስቃሴ የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን ለማለፍ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ጠቁመው፤ የመልካም አስተደደር ችግሮች እልባት እንዲያገኙ የሚጠበቅብንን ድርሻ መወጣት አለብን ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡ ከአገልግሎት አሰጣጥ አኳያም ከህዝቡ የሚነሱ ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የኢኮኖሚ ክላስተር ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት ለመሆን ያስቀመጠችው ግብ በትክክለኛ መስመር ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡   የተፈጥሮ ጋዝ፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረጉ ፕሮጀክቶች ለዚህ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን አስታውሰው፤ ይህም የኢትዮጵያ ልዕልና ከፍ እያለ ለመምጣቱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ ለማላቅ ርብርብ እንደሚጠይቅ ጠቁመው፤ ሀገራዊ ኢኒሼቲቮች ግባቸውን እንዲመቱ ተሳትፏችን ይበልጥ ሊጎላ ይገባል ነው ያሉት፡፡ የእውቅና መርሃ ግብሩ በወረዳዎች መካከል በአፈፃፀም ዙሪያ ልምድ ልውውጥ ለማድረግና የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ትልቅ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያን ክብርና ሉአላዊነት በላቀ ብቃትና ዝግጁነት የማስጠበቅ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ
Oct 8, 2025 161
ባሕርዳር ፤ መስከረም 28/2018 (ኢዜአ) ፡- የኢትዮጵያን ክብርና ሉአላዊነት በላቀ ብቃትና ዝግጁነት የማስጠበቅ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ ገለጹ። ሌተናል ጄኔራሉ በየደረጃው ካሉ የዕዙ ከፍተኛ መኮንኖችና ኃላፊዎች ጋር በመምከር በግዳጅ አፈጻጸም ቀጣይ ተልዕኮዎችን በተመለከተ አቅጣጫ ሰጥተዋል።   የኢትዮጵያ የጀግንነት ታሪክ ከጥንት ጀምሮ አብሮ የዘለቀ እና አሁንም በላቀ መልኩ የቀጠለ መሆኑን አንስተው፤ የሰራዊቱ ጀግንነት፣ ግዳጅና ተልዕኮ የመፈፀም ብቃት የሚደነቅ ነው ብለዋል። በእድገትና ማንሰራራት እንዲሁም ስኬቶችን እያስመዘገበች ለቀጠለችው ኢትዮጵያ የሚመጥን ጠንካራ ሰራዊት መገንባቱን አንስተው፤ ክብርና ሉአላዊነቷን አስጠብቆ መዝለቅ የዚህ ትውልድ አደራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የቀደሙት አያቶች አኩሪ የጀግንነት ገድል ከነ ሙሉ ክብሯ ያስረከቡንን ሀገር እኛም በላቀ ክብርና ሞገስ ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ግዴታ አለብን ብለዋል። በኢትዮጵያ ለጠላት አስፈሪና ለሀገር አኩሪ የሆነ ጠንካራና ዘመናዊ ሰራዊት መገንባቱን ያነሱት ሌተናል ጀነራል መሐመድ፤ በዚህ ረገድ የምስራቅ ዕዝ የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት ለማስጠበቅ ለላቀ ሀገራዊ ተልእኮ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በጫካ የሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን በክህደት የጠላት ተልዕኮ ለማስፈፀም ቢሞክርም በዕዙ ጠንካራ እርምጃ እየተወሰደበት መሆኑን አረጋግጠዋል። የምስራቅ እዝ በዚሁ የግዳጅ አፈፃፀም ጽንፈኛ ቡድኑን በመከታተል እርምጃውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸው፤ በክልሉ ዘላቂ ሰላምን ለማፅናት ወታደራዊ እርምጃው የሚቀጥል መሆኑንም አፅንኦት በመስጠት አብራርተዋል። ዋና አዛዡ እንዳመለከቱት፤ ከአማራ ክልል የፀጥታ ሀይል ጋር በመጣመር የሚደረጉት ስምሪቶች ውጤት ማምጣታቸውን አስታውሰው፣ በአሁኑ የክልሉ የፀጥታ ሀይል ራሱን ችሎ በመንቀሳቀስ አኩሪ ግዳጅ እየፈጸመ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል ። በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን ዓላማ የኢትዮጵያን ጠላቶች ተልእኮ በመቀበል ሀገርና ህዝብን መውጋት መሆኑን ህዝቡ በአግባቡ የተረዳ በመሆኑ ከሰራዊቱ ጎን በመቆም አጋርነቱን እያሳየ መሆኑን እና ሰራዊቱ ተከታትሎ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ገልጸዋል ።
ስፔን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ትብብር አጠናክራ ትቀጥላለች -አምባሳደር ጉሌርሞ ሎፔዝ
Oct 8, 2025 153
አዲስ አበባ፤ መስከረም 28/2018(ኢዜአ)፡- ስፔን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል በኢትዮጵያ የስፔን አምባሳደር ጉሌርሞ ሎፔዝ ማክ-ሌላን ገለፁ። በኢትዮጵያ የስፔን አምባሳደር ጉሌርሞ ሎፔዝ ማክ-ሌላን ስፔን ከኢትዮጵያ ጋር ለረጅም ጊዜያት በተለያዩ ዘርፎች በጋራ እየሰራች ነው ብለዋል። ሁለቱ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና በሌሎች የልማት ስራዎች በጋራ እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል። በስፔን ትብብር ማዕቀፍ በኩል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማረጋገጥና ለማብቃት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም በርካታ ሴቶች በኢትዮጵያ የልማት ጉዞ ውስጥ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል። በጤናው ዘርፍ ከህክምና መሳሪያዎች ጀምሮ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት የሚያስችል ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ልማትን ለማረጋገጥ ለምታደርገው ጥረት ስፔን ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ነው ያስረዱት። በሌላ በኩል ስደተኞችና ተቀባዩ ማህበረሰብ የንፁህ ውሃ አቅርቦት፣ የሶላር ኢነርጂና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት እንዲያገኙ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እየሰራን ነው ብለዋል። ስፔን በቀጣይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።
ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታን አጎልብቶ ለማስቀጠል የመደመር መንግስት መጽሐፍ ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል- ምሁራን
Oct 8, 2025 154
ሆሳዕና ፤ መስከረም 28/2018(ኢዜአ)፡- ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታን አጎልብቶ ለማስቀጠልና ሁለንተናዊ እድገትን ለማፋጠን የመደመር መንግስት መጽሐፍ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ምሁራን ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው ''የመደመር መንግሥት'' የተሰኘው መጽሀፍ ተመርቆ ለንባብ መብቃቱ ይታወሳል፡፡ በመጽሐፉ ዙሪያ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን እንዳመለከቱት፤ መጽሃፉ ያለፈውን ከመጪው ዘመን ጋር ያዋሀደ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታን ለመፍጠር የሚደረግ ጥረትን የሚያሳይ ነው፡፡ በዩኒቨርሲቲው የታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት መምህር አስራት ኤርሞሎ፤ የመደመር መንግሥት መፅሐፍ ሀገር በቀል እዉቀትን መሰረት አድርጎ የሀገሪቱን ባሕልና እሴትን በጠበቀ መልኩ እንደተዘጋጀ መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ከነበሩ የተለያዩ የመንግሥት ስርዓቶች መልካም እሴቶችን በተሞክሮነት በመዉሰድ ለሀገረ መንግሥት ግንባታዉ መጠናከር እና መጠቀም ከዚህ ቀደም እንዳልታዩ አስታውሰው፤ መልካምን እሴት ባሕል አደርጎ ማስቀጠል ተገቢ መሆኑ አስረድተዋል፡፡ የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ፍልስፍና መልካሙን እሴት ጠብቆ ጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታን አጎልብቶ ለማስቀጠል ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል ። መጽሀፉ ሀገራዊ አንድነትን ከማጠናከር በተጨማሪ ለቀጣናዉ ትስስር፣ሰላም፣ለጋራ እድገትና ብልፅግና መረጋገጥ ጭምር ጉልህ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባም ያሳየ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ያለንን የተፈጥሮ ሀብቶች በአግባቡ በመጠቀም ኢንቨስትመትን መሳብና ማበረታታት እንዲሁም ሀገሪቱ የውጭ ባለሀብቶችን በመሳብ ማዕከል እንድትሆን በማድረግ የኢኮኖሚ ዕድገትን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ማፍጠን የሚያስችሉ ሀሳቦች የያዘ መሆኑን መመልከታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሌላኛዉ በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት መምህር አቶ አበራ ሄቢሶ በበኩላቸው፤ የመደመር መንግሥት መጽሀፍ የሀገራችንን የዘመናት ቆይታንና ያልተመጣጠነ እድገትን በቁጭት ያመላከት ነው ብለዋል፡፡ ለሀገርና ለዜጎች ሁለንተናዊ እድገትና ተጠቃሚነት መረጋገጥ በጊዜ የለንም መንፈስ መስራት እንደሚገባ የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በማመላከት ትምህርት የሚሰጥ መጽሐፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለአብሮነታችን ቅድሚያ በመስጠት ከዚህ ቀደም በተለያያ ምክንያቶች የባከኑብንን ጊዜያት ለአንድ ዓላማ በመሰለፍ መካስ እንደሚገባንና በዚህም መጪው ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ስራ ለማከናወን በርካታ እድሎች መኖራቸውን ያሳየ ነው ያሉት፡፡ ከሁሉ በላይ የኢትዮጵያዊነት እሴት ጎልቶ እንዲወጣ በማድረግና የሀሳብ ልዕልናን በማስቀደምና በመትጋት ስኬቶችን ከወዲሁ ማምጣት እንደሚቻል ያመላከተ መጽሐፍ ስለመሆኑ ጠቅሰዋል፡፡ ለሀገራችን ብልፅግና መረጋገጥ በጋራ እንድንተጋ ጭምር አቅጣጫ የሚያመላክት ከመሆኑም ባለፈ አብሮነትና አንድነት ውስጥ ያለውን ሀይል በማቀናጀት መልማትና ማደግ እንደሚቻል ብሩህ ተስፋን የሰነቀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመጽሀፉ የተቀመጡ ዕውነታዎች ወደ ተግባር እንዲለወጡ ከማንበብ ባሻገር በጊዜ የለንም መንፈስ ተግቶ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡    
የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ጥያቄዎች ሕገ-መንግስታዊና ሕጋዊ አሰራርን በተከተለ አግባብ ምላሽ እንዲያገኙ ይደረጋል
Oct 8, 2025 168
አዲስ አበባ፤ መስከረም 28/2018(ኢዜአ)፦ የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ጥያቄዎች ሕገ-መንግስታዊና ሕጋዊ አሰራርን በተከተለ አግባብ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ምላሽ እንዲያገኙ እንደሚደረግ በፌዴሬሽን ምክር ቤት የማንነት፣ የአስተዳደር ወሰንና የሰላም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት በ6ኛ የፓርላማ ዘመን 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ 1ኛ መደበኛ ስብሰባ የማንነት፣ አስተዳደር፣ ወሰንና ሰላም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴ የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃጸም ሪፖርትን በማዳመጥ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ተወያይቶ አጽድቋል።   የቋሚ ኮሚቴው ጸሐፊ አቶ ፍቅሬ አማን፥ በህዝቦች በሚቀርቡ የማንነት፣ አስተዳደር ወሰንና ሠላም ግንባታ ጉዳዮች ላይ የተከናወኑ ተግባራት ከዚህ ቀደም ከሚቀርቡት አንፃር ሲታይ እየቀነሱ ነው ብለዋል። በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ለሚቀርቡ የማንነት ይታወቅልኝና የህዝብ ውክልና አቤቱታዎች በጥናት ላይ የተመሰረተ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል። የብሔር፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች የማንነት መገለጫ (አትላስ) ጥናትን ለማስጀመር ከባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመሩ የምክክር መድረኮችን በማስቀጠል ቀሪ ተግባራት በማጠናቀቅ ወደስራ እንደሚገባም ተናግረዋል። በአስተዳደር ወሰንና እራስን በራስ የማስተዳደር የሚነሱ ጥያቄዎች ሕገ-መንግስታዊና ሕጋዊ አሰራርን በተከተለ አግባብ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ምላሽ እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል። በሁሉም ክልሎች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትንና የሰላም እሴት ግንባታ ስራዎችን የሚያጠናክሩ የምክክር መድረኮች በስፋት ለማካሄድ መታቀዱንም አስረድተዋል። በምክር ቤቱ ቀርበው የነበሩና ወደክልሎች የተላኩ አቤቱታዎችን አፈፃፀም በመገምገም የድጋፍና ክትትል ስራዎችን በማከናወን ህዝቦች የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል። የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ የማንነት ይታወቅልኝና የአስተዳደር ወሰን ጥያቄዎች ከጊዜ ወደጊዜ እየቀነሰ መምጣቱ መንግስት የህዝቦችን ጥያቄ ተገቢ የመልካም አስተዳደር ምላሽ እየሰጠ መሆኑን የሚሳይ እንደሆነ ገልጸዋል። በቀጣይም በአማራና ትግራይ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና ሲዳማ፣ በጋምቤላና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሚነሱ የማንነትና የአስተዳደር ወሰን ጥያቄዎች የህዝብን አንድነት በሚያጠናክር መልኩ ምላሽ እንዲያገኙ መስራት እንደሚያስፈልግ ጠይቀዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እና የማንነት፣የአስተዳደር ወሰንና የሰላም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጥላሁን ከበደ፥ የተፈጸሙ፣ ያልተፈፀሙና ለግጭት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት የማንነት፣አስተዳደር፣ ወሰንና ሰላም ግንባታ ስራዎችን ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ህዝቦች የሚያነሷቸው ጥያቄዎች አንድነትና ወንድማማችነትን በሚያጠናክር መልኩ ሕገመንግስታዊና ህጋዊ ምላሽ እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል። በፌዴሬሽን ምክር ቤት የማንነት፣የአስተዳደር ወሰንና የሰላም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ አቶ ፍቅሬ አማን፥ በአማራና ትግራይ አዋሳኝ አካበቢዎች የሚነሳውን የማንነትና የአስተዳደር ወሰን ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በመንግስት ደረጃ ግልጽ አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራበት ነው ብለዋል። በሁሉም አካባቢዎች የሚነሱ የማንነትና የአስተዳደር ወሰን ጉዳዮችን ሕጋዊና ሕገ-መንግስታዊ አሰራርን በተከተለ አግባብ ምላሽ የመስጠት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚያጎለብቱ ተግባራት ትኩረት ተሰቷቸዋል- አቶ አገኘሁ ተሻገር
Oct 8, 2025 96
አዲስ አበባ፤ መስከረም 28/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚያጎለብቱ ተግባራት ትኩረት እንደተሰጣቸው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት በ6ኛ የፓርላማ ዘመን 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ 1ኛ መደበኛ ስብሰባ የመንግስታት ግንኙነት፣ ዴሞክራሲያዊ አንድነትና የሕገ-መንግስት አስተምህሮ ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም የሕገ መንግስትና የፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምን በማዳመጥ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ተወያይቶ አጽድቋል።   በፌዴሬሽን ምክር ቤት የመንግሥታት ግንኙነት፣ የዴሞክራሲያዊ አንድነትና የሕገ መንግሥት አስተምህሮ ቋሚ ከሚቴ ጸሐፊ ወይዘሮ ባንችይርጋ መለሰ÷ 19ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ሕብረብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ በአርባ ምንጭ ከተማ በድምቀት መከበሩን አስታውሰዋል።   በቀጣይም የፌደራል ሥርዓቱ ጤናማነቱ የተረጋገጠና ተቋማዊነቱ የተጠናከረ እንዲሆን የሚያስቸል ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም ዙሪያ የዜጎችን ግንዛቤ በማሳደግ ብሔራዊ መግባባትና የህዝቦችን አንድነት የሚያጎለብቱ የአስተምህሮ ስርጸት ተግባራት ትኩረት እንደሚሰጣቸው አስረድተዋል። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ብዝኃነት ላይ የተመሰረተ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጎላ መልኩ በድምቀት ማክበር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። ክብረ በዓሉ የህዝቦችን የነቃ ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ በሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበርና በሀገር አቀፍ ደረጃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እንደሚከበር አስተረድተዋል።   በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግስትና የፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ኃይለ ኢየሱስ ታዬ (ዶ/ር)÷ ባለፈው ዓመት በትምህርት ተቋማትና በመገናኛ ብዙኃን የፌደራሊዝም አስተምህሮ ተግባራት መከናወኑን ገልጸዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም በጥናትና ምርምር፣ በፌደራሊዝምና ሕገ-መንግስታዊ አስተምህሮ የዜጎችን ግንዛቤ የሚያሳድጉ ተግባራት እንደሚከናወኑ አስገንዝበዋል። የምክር ቤቱ አባል ወንዳለ ሀብታሙ (ዶ/ር)÷ በመንግስታት ግንኙነት፣ በሕገ መንግስትና የፌደራሊዝም አስተምህሮ የዜጎችን ህብረ ብሔራዊ አንድነት የሚያስጠብቁ ተግባራት መጠናከር ይኖርባቸዋል ብለዋል።   የዜጎችን አንድነት ለማጠናከርም በሕገ መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል በኩል ኪነ-ጥበብንና የትምህርት ሥርዓቱን በመጠቀም ግንዛቤን ማሳደግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር በማጠቃለያቸው÷ ኢትዮጵያ በማንሰራራት ዘመን ጉዞ ላይ ናት ብለዋል። የዜጎችን ሕብረ ብሔራዊ መግባባትና አንድነት የሚያጎለብቱ የአስተምህሮና የስርጸት ተግባራት በትኩረት እንደሚሰራባቸው አንስተዋል። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ታላላቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች በሚከወኑበት ወቅት የሚከበር በመሆኑ ልዩ ትርጉም እንደሚሰጠው ተናግረዋል። በዓሉ ህብረ ብሔራዊነትን በማጎልበት የሀገርን የማንሰራራት ጉዞ በሚያሳካ መልኩ በልዩ ድምቀት እንደሚከበር ጠቅሰዋል።  
በፌደራል መንግስት የሚገነቡ መሰረተ ልማቶችን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥ ጥብቅ ክትትል እየተደረገ ነው
Oct 7, 2025 194
አዲስ አበባ፤ መስከረም 27/2018 (ኢዜአ)፦ በፌደራል መንግስት ባለቤትነት የሚገነቡ የመሠረተ ልማት አውታሮችን ሥርጭት ፍትሐዊነት ለማረጋገጥ ጥብቅ ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት የተለያዩ ቋሚ ኮሚቴዎችን የዕቅድ አፈፃጸምና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ በ6ኛ የፓርላማ ዘመን 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ 1ኛ መደበኛ ስብሰባ በተያዙ ስምንት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ አጽድቋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር÷ የመረጃንና ማስረጃ የአሰራር ሥዓትን የተከተለ የፌደራል መንግስት የድጎማ በጀት ትልልፍ ሥርዓትን የማጠናከር ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። የፌደሬሽን ምክር ቤት ፍትሐዊ የመሰረተ ልማት ሥርጭትን ለማረጋገጥ ጥብቅ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመው÷ ለዚህም የመሰረተ ልማት ስርጭት ፍትሐዊነት ማረጋገጫ መስፈርት በማውጣት እየተሰራበት እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። የበይነ መንግስታት የፊስካል ሽግግሮችን በፍትሐዊነትና ውጤታማነት ለማጠናከርም የቋሚ ኮሚቴ አባላት እያበረከቱት ያለውን ገንቢ ድጋፍ አጠናክረው መቀጠል እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል። አዳዲስ ክልሎችም የህዝባቸውን የልማት ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት የሚያስመዘግቡትን እመርታዊ ስኬት አጠናክረው ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። በፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ አቶ ኃይሉ ኢፋ ÷ የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን እንደመነሻ በመውሰድ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል። የበይነ መንግስታትን የፊስካል ሽግግር ፍትሕዊነትና ውጤታማ የማስፈጸም አቅም በማጎልበት የድጎማና የጋራ ገቢዎች አስተዳደርና የማካፈያ ቀመርን የመከታተልና የመደገፍ ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል። የፌደራል የመሠረተ ልማት አውታሮች ሥርጭት ፍትሐዊነትና ውጤታማነት ክትትል አቅምን የማሳደግ ስራም በበጀት ዓመቱ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም ልዩ ዓላማ ያላቸው የፌደራል ድጎማዎች በግልጽነት፣ ተጠያቂነትና ዘላቂ የአሰራር ሥርዓት ለክልሎች መከፋፈላቸውን የማረጋገጥ ስራ ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ ተናግረዋል። የመንግስታት ፊስካል ሽግግሮችን ፍትሐዊነትና ውጤታማነት በጋራ ገቢዎች አሰባሰብ፣ አስተዳደርና ትልልፍ ሂደት ጉልህ ስኬት እየተገኘበት መሆኑን አስረድተዋል። ለአብነትም በ2012 በጀት ዓመት 4 ነጥብ 2 ቢሊየን የነበረው የክልሎች ድርሻ በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ወደ 91 ነጥብ 73 ቢሊዮን ብር ማደጉን አብራርተዋል። በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የበይነ መንግስታትን ፊስካል ሽግግሮችን በፍትሐዊነትና በውጤታማነት በመምራት የፌደራል መሠረተ ልማት አውታሮች ክልላዊ ሥርጭት በተዘረጋው የአሰራር ሥርዓት መፈጸሙን ማረገገጥ የትኩረት መስክ መሆኑን አስረድተዋል። የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ የክልሎችን የዕድገት ደረጃ ተመጣጣኝነት ለማረጋገጥ እየተተገበረ ባለው አሰራር የፊስካል ሽግግሮች ፍትሐዊነትና ውጤታማነት ከፍተኛ ውጤት መምጣቱን ገልጸዋል። በአዲስ መልክ ለተደራጁ ክልሎችም ለ2018 በጀት ዓመት የድጎማ በጀት ማከፋፈያ ቀመሩ ተግባራዊ የሚሆንበት ሥርዓት እንዲፈጠር ጠይቀዋል። የፌደራል መሠረተ ልማት አውታሮች ክልላዊ ሥርጭትና በግንባታ ሂደት የሚስተዋሉ የአፈፃፀም ግድፈቶች ላይ በጥብቅ ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠይቀዋል። በፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ አቶ ኃይሉ ኢፋ በምላሻቸው÷ ውስን ዓላማ ባላቸው የፌደራል መንግስት ድጎማዎች ትልልፍና ክትትል የተመዘገበው ውጤት ተጠናክሮ ቀጥላል ብለዋል። የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ አሻድሊ ሀሰን÷ የጋራ ገቢና ለክልሎች የሚደረገው ትልልፍ ዕድገት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። አዳዲስ ክልሎችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች የአሰራር ሥርዓትን በተከተለ አግባብ ተመጣጣኝና ፍትሐዊ የመሠረተ ልማት ሥርጭትን ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በ6ኛ የፓርላማ ዘመን 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ 1ኛ መደበኛ ስብሰባው የፌዴሬሽን ምክር ቤት የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ዕቅድ በሙሉ ድምጽ ጽድቋል። በመጨረሻም የሕገ-መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ የሕገ-መንግሥት ትርጉም ያስፈልጋቸዋል በማለት በ13 ጉዳዮች ላይ ያቀረባቸውን የውሳኔ ሃሳቦች መርምሮ ለምክር ቤቱ በማቅረብ አስጸድቋል።
በደሴ የሰፈነውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራው የበለጠ እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፉ ይጠናከራል- ምክር ቤቱ
Oct 7, 2025 125
ደሴ፤ መስከረም 27/2018(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ የሰፈነውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራው የበለጠ እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፉን እንደሚያጠናክር የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት ገለጸ። በከተማው የሚካሄዱ የደሴ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 44ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው። የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባዔ አቶ አህመድ ሙህዬ በጉባዔው መድረክ ባደረጉት ንግግር፤ በከተማው የሰፈነውን ሰላምን በማፅናት የልማት ተግባራት እንዲፋጠኑ ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።   በዚህም በከተማው ሰላምን በማስጠበቅ በመሰረተ ልማት፣ በጽዳትና ውበት ጨምሮ በሌሎችም ዘርፎች ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን በክትትል ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል። በከተማው ታይቶ የማይታወቅ ልማት እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የምክር ቤት አባል ወይዘሮ ሰርካለም አበበ ናቸው። ሕብረተሰቡ አንድነቱን በመጠበቅ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ፈጥነው እንዲጠናቀቁ ክትትልና ደጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።   ሌላው የምክር ቤቱ አባል አቶ ቴዎድሮስ አድማሴ፤ በከተማው በተለያዩ ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ አበረታች ውጤቶች እንዲቀጥሉ እያደረግን ያለውን ድጋፍና ክትትል እናጠናክራለን ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው፤ ሕብረተሰቡን በማስተባበር የከተማዋን ሰላም ከመጠበቅ ባለፈ ሰፋፊ የልማት ስራዎች ሲከናወኑ እንደቆዩ አውስተዋል።   በዚህም በኮሪደር ልማት፣ በስራ እድል ፈጠራ፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በመሰረተ ልማት፣ በመልካም አስተዳደርና ገበያ በማረጋጋት አበረታች ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። የተጀመሩትን ፈጥኖ በማጠናቀቅና አዳዲስ የልማት ስራዎችን በማስጀመር የሕዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማጎልበት የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱም ለተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች አንድ ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር ተመድቦ ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመው፤ የሕብረተሰቡን ተሳትፎና ትብብር በማከል ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ይሰራል ብለዋል። ዛሬ ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚቆየው የምክር ቤቱ ጉባዔ የምክር ቤቱ አባላትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
በኢትዮጵያ የተገነባው ዘመናዊና ጠንካራ ሰራዊት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት በአስተማማኝ መልኩ የሚጠብቅ ነው-ጄኔራል አበባው ታደሰ
Oct 7, 2025 190
ባቱ ፤መስከረም 27/2018(ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ የተገነባው ዘመናዊና ጠንካራ የመከላከያ ሰራዊት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት በአስተማማኝ መልኩ የሚጠብቅ መሆኑን የጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ ገለጹ። የሀገር መከላከያ ሰራዊት የደቡብ ዕዝ 21ኛ ጉና ክፍለ ጦር 30ኛ የምስረታ በዓል በኦሮሚያ ክልል ባቱ ከተማ ከፍተኛ ወታዳራዊ መኮንኖች፣የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና ሌሎችም ታዳሚዎች በተገኙበት ተከብሯል።   በዚሁ ሁነት ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ፤የሀገር መከላከያ ሰራዊት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣በብቃትና ጀግንነቱ ጭምር የኢትዮጵያ አስተማማኝ አለኝታ መሆኑን ገልጸዋል። የውስጥ ባንዳዎችንና የውጭ ጠላቶችን ከንቱ ህልሞች በማምከን ኢትዮጵያ ተከብራና ሉአላዊነቷ ተከብሮ እንድትዘልቅ ያደረገ መሆኑንም አንስተዋል። በኢትዮጵያ የተገነባው ዘመናዊና ጠንካራ ሰራዊት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት በአስተማማኝ መልኩ የሚጠብቅ ነው ሲሉም አረጋግጠዋል። የደቡብ ዕዝ 21ኛ ጉና ክፍለ ጦር ባለፉት 30 ዓመታት ሰላምና ደህንነትን ከማረጋገጥ ባለፈ በርካታ ወታደራዊ መሪ ያፈራና ትምህርታዊ ልምድ የተወሰደበት የሰራዊት ክፍል መሆኑንም አንስተዋል።   የደቡብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሰለሞን ኢተፋ፥ ክፍለ ጦሩ የፀረ ሰላም ሃይሎችን የሽብር እንቅስቃሴ በማክሸፍ አኩሪ ገድል በመፈፀም ሀገርን በማፅናት በኩል የላቀ ሚናውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። ክፍለ ጦሩ የተለያዩ ክፍለ ጦሮች እንዲመሰረቱ ልምድና መሰረት በመሆን እያገለገለ መሆኑንም ተናግረዋል። የባቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አህመዲን እስማኤል ፤ የከተማዋና አከባቢዋ ሕብረተሰብ የኢትዮጵያ ጥንካሬ መገለጫ ከሆነው የሀገር መከላከያ ጎን ነው ብለዋል። የአካባቢው ሕብረተሰብ ሰላምን በማፅናት ልማትና ዕድገት በተሻለ ደረጃ እያስቀጠለ ነው ያሉት ከንቲባው፥ባቱና የአካባቢዋ ማህበረሰብ ሰላሙን በመጠበቅ ረገድ ከሀገር መከላከያና ከፀጥታ አካላት ጋር በትብብር በመስራት ሰላምን በማረጋገጥ የበኩላቸውን እንደተወጡ ገልጸዋል። በክበረ በዓሉ ላይ የሀገር ህልውና በማስጠበቅ ላይ ለተሰውና በክብር ለተሰናበቱ የክፍለ ጦሩ አባላት ቤተሰቦች እውቅና ተሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም