ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የአፋሕድ ምክትል ሊቀመንበር ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ የሰላም አማራጭን ተቀበሉ
Jan 12, 2026 25
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ምክትል ሊቀመንበር እና ወታደራዊ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ ከእነ ሠራዊታቸው የሰላም አማራጭን ተቀብለው ገብተዋል። ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ አፋሕድ ከአማራ ክልል መንግሥት ጋር በአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ አማካኝነት ያደረገውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የሰላም ስምምነቱን በመቀበል ከነሠራዊታቸው መግባታቸውን አሚኮ ዘግቧል። በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና በአፋሕድ መካከል ሕዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።
የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት ነው
Jan 12, 2026 21
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት መሆኑን አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። አምባሳደር ሌንጮ ባቲ በኮንፍረንሱ ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ የጋራ ትርክት መገንባት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ልዩነቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ በማምጣት መወያየትና መነጋገር እንደሚገባ ጠቁመው፤ ምክክር ማድረግ ሁነኛ አማራጭ ነው ብለዋል። አንድነትን፣ አብሮነትንና እኩልነትን የሚያጎላ ትርክት መቅረጽ እንደሚገባም ተናግረዋል። የሚያስተሳስሩ እና ዘመን ተሻጋሪ አብሮነቶችና ትስስሮችን ማጉላት የሚያስችል ትርክትን መገንባት እንደሚገባም ገልጸዋል። የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመችና የበለጸገች ኢትዮጵያን መፍጠር መሆኑንም አንስተዋል። "ሀገራዊ ማንነት፣ የጋራ ትውስታዎችና የሀገረ መንግሥት ቅቡልነት፤ የኢትዮጵያ ተሞክሮ እና የመገናኛ ብዙኃን ሚና" በሚል ርዕስ ጽሑፍ ያቀረበችው ሙኒራ አብዱልመናን መገናኛ ብዙኃን የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በማሳለጥና የዜጎችን የጋራ ማንነት በመቅረጽ ረገድ የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ተናግራለች። መገናኛ ብዙሃን ከአግላይና ነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ የወል ትርክቶችን እና እሴቶችን ማጉላት እና ማስተጋባት እንደሚገባቸው ገልጻለች። መገናኛ ብዙኃን ለብሔራዊ መግባባት ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባም ጨምራ ተናግራለች። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችም ስለ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸው ግንዛቤ ሊያድግ እንደሚገባ በመግለጽ፤ ለትውልድ የሚሻገር አስተሳሳሪ ትርክት ለመገንባት መትጋት እንደሚገባቸውም አንስታለች። በመድረኩ በኢትዮጵያ የጋራ ትርክትን ተቋማዊ ለማድረግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ሰፊ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ የሚያጸኑ አስደማሚ የልማት ስኬቶች እየተመዘገቡ ነው
Jan 12, 2026 40
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ የሚያጸኑ አስደማሚ የልማት ስኬቶች መመዝገባቸውን የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የበጀት ዓመቱን ያለፉት ስድስት ወራት የልማት አፈፃጸም አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፥ 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዓመት ነው ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራትም የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያጸኑ አስደማሚ የልማት ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህም በብዝኅ የኢኮኖሚ ዘርፍ በ2030 ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት የሚያደርጉ የልማት ስኬቶች እየተመዘገቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት የጉባ ብስራት ፕሮጀክቶች ጅማሮም ኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ጀምራ ማጠናቀቅ እንደምትችል የሚያሳዩ መሆናቸውን አብራርተዋል። ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካና የዓለም የአየር ትራንስፖርት ፋና ወጊ በማድረግ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማሪፊያ ግንባታ መጀመር የንግድ ትስስርን ለማሳለጥ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው በአብነት ጠቅሰዋል። የመደመር መንግሥት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያም በሁሉም መስኮች ችግሮችን በማረም የኢትዮጵያን ዕድገት የሚያሳልጥ ውጤት መመዝገቡን አብራርተዋል። በዚህም በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና ዲጂታል ብዝኅ የኢኮኖሚ መስኮች እመርታዊ ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት እሳቤ በግብርና መስክ በበጋ መስኖ ስንዴ፣ በኩታ ገጠምና በሌማት ትሩፋት የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት በማረጋገጥ ተመጽዋችነትን የሚገታ የምርት ውጤት እየተገኘ መሆኑን አንስተዋል። የጉባ ብስራት ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅም ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ ጠቅሰዋል። ከተሞችን የብልጽግና ማዕከል ለማድረግ በአዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማትም በበርካታ ከተሞች በስፋት እየተሰራበት መሆኑን ገልጸዋል። በዲፕሎማሲ መስክም በአሕጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረኮች የኢትዮጵያ ተሳትፎም ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ የአፍሪካ ድምጽ መሆን ያስቻለ ስኬት መመዝገቡን ተናግረዋል። በመንግስትና ሕዝብ መካከል የተደረጉ መድረኮችም ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የልማት ስኬት ዕውቅና የተሰጠበት መሆኑን አብራርተዋል። በዚህ ዓመት የሚካሄዱት የሀገራዊ ምክክርና ሀገራዊ ምርጫ ዐበይትና ወሳኝ ሁነቶችን በአሳታፊነት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ በስኬት ለማስኬድም መንግስት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በአብዛኛው የኢትዮጵያ አካባቢዎች ደረቅና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jan 12, 2026 22
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በአብዛኛው የኢትዮጵያ አካባቢዎች ደረቅና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ አንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፣በሚቀጥሉት አሰር ቀናት አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ክፍሎች ደረቅና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሀዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል። የበጋው ደረቅ ጸሃያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች እንደሚስተዋልና የለሊትና የማለዳው ቅዝቃዛ ከአምስት ዲግሪ ሼልሲየስ በታች እንደሚሆን አመልክቷል። ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑ የደቡብና የደቡብ ምስራቅ አካባቢዎችደረቅ ሆነው እንደሚቆዩም የትንበያ መረጃው ያመለክታል። በሌላ በኩል በደቡብ ምዕራብ፣የምዕራብና የመካከለኛው እንዲሁም ሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ አንጻራዊ የእርጥበት መጠንና የደመና ሽፋን ጥንካሬ ሊኖራቸው እንደሚችል በትንበያው ተመላክቷል።
ከክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት 33ሺህ 700 ቶን የቡና፣ ሻይ እና ቅመማቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል
Jan 12, 2026 51
ቦንጋ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል 33ሺህ 700 ቶን የቡና፣ ሻይ እና ቅመማቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡ ተመለከተ። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ የሺዋስ ዓለሙ፤ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትንና ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል። በተለይም በግብርናው ዘርፍ በዋና ዋና ሰብሎች እንዲሁም በቡና፣ ሻይ እና ቅመማቅመም ምርቶች ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በዚህም መሰረት በክልሉ በዋና ዋና ሰብሎች 384 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት ከ20 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት 33 ሺህ 700 ቶን የቡና፣ ሻይ እና ቅመማቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን ጠቁመው ከቀረበው ውስጥ 13ሺህ ቶኑ ቡና፣ 2ሺህ 700 ቶኑ ሻይ እና 18 ሺህ ቶኑ ቅመማቅመም መሆኑን አመልክተዋል። በሌላ በኩል በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ255 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መቅረቡንም ጠቁመዋል። በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ አገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች ለተሰማሩ 52 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል። በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርም በርካቶች ተሰማርተው ስኬታማ መሆናቸውንና ለሌሎችም ጭምር የስራ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል። የውሃ፣ የመስኖ፣ የመንገድና ድልድዮችን፣ እንዲሁም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ መሰረተ ልማቶች መከናወናቸውን ተናግረዋል። በተለይም በከተሞች ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል አገልግሎት በመስጠት በኩል መልካም ጅምሮች መኖራቸውን አንስተው በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ፖለቲካ
የአፋሕድ ምክትል ሊቀመንበር ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ የሰላም አማራጭን ተቀበሉ
Jan 12, 2026 25
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ምክትል ሊቀመንበር እና ወታደራዊ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ ከእነ ሠራዊታቸው የሰላም አማራጭን ተቀብለው ገብተዋል። ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ አፋሕድ ከአማራ ክልል መንግሥት ጋር በአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ አማካኝነት ያደረገውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የሰላም ስምምነቱን በመቀበል ከነሠራዊታቸው መግባታቸውን አሚኮ ዘግቧል። በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና በአፋሕድ መካከል ሕዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።
የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት ነው
Jan 12, 2026 21
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት መሆኑን አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። አምባሳደር ሌንጮ ባቲ በኮንፍረንሱ ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ የጋራ ትርክት መገንባት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ልዩነቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ በማምጣት መወያየትና መነጋገር እንደሚገባ ጠቁመው፤ ምክክር ማድረግ ሁነኛ አማራጭ ነው ብለዋል። አንድነትን፣ አብሮነትንና እኩልነትን የሚያጎላ ትርክት መቅረጽ እንደሚገባም ተናግረዋል። የሚያስተሳስሩ እና ዘመን ተሻጋሪ አብሮነቶችና ትስስሮችን ማጉላት የሚያስችል ትርክትን መገንባት እንደሚገባም ገልጸዋል። የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመችና የበለጸገች ኢትዮጵያን መፍጠር መሆኑንም አንስተዋል። "ሀገራዊ ማንነት፣ የጋራ ትውስታዎችና የሀገረ መንግሥት ቅቡልነት፤ የኢትዮጵያ ተሞክሮ እና የመገናኛ ብዙኃን ሚና" በሚል ርዕስ ጽሑፍ ያቀረበችው ሙኒራ አብዱልመናን መገናኛ ብዙኃን የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በማሳለጥና የዜጎችን የጋራ ማንነት በመቅረጽ ረገድ የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ተናግራለች። መገናኛ ብዙሃን ከአግላይና ነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ የወል ትርክቶችን እና እሴቶችን ማጉላት እና ማስተጋባት እንደሚገባቸው ገልጻለች። መገናኛ ብዙኃን ለብሔራዊ መግባባት ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባም ጨምራ ተናግራለች። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችም ስለ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸው ግንዛቤ ሊያድግ እንደሚገባ በመግለጽ፤ ለትውልድ የሚሻገር አስተሳሳሪ ትርክት ለመገንባት መትጋት እንደሚገባቸውም አንስታለች። በመድረኩ በኢትዮጵያ የጋራ ትርክትን ተቋማዊ ለማድረግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ሰፊ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Jan 12, 2026 42
ጋምቤላ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። የጋምቤላ ክልል የመንግስት ሰራተኞች በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ የውይይት መድረክ አካሂደዋል። በውይይት መድረኩ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ፤ በክልሉ የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት የመንግስት ሰራተኞች ተሳትፎ እና ትብብር ወሳኝ መሆኑን አንስተው በሁሉም ረገድ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠልና የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የሚነጣጥሉ እሳቤዎችን በመተው አሰባሳቢና የወል ትርክቶችን በመገንባት ረገድም የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ የሚጥሩ አካላትን በመከታተል በህግ ተጠያቂ የማድረግ፣ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥና የልማት ስራዎችን ለስኬት የማብቃት ጉዳይ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ይሰራል ብለዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) የክልሉ መንግስት የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ የልማት ስራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም የሁሉም ድጋፍና ትብብር አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በተለይም የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ አስገንዝበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን፤ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በማጠናከር ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ልንቆም ይገባል ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች መሳካት የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በጋምቤላ ክልል ለልማት የሚውል እምቅ የተፈጥሮ ሀብት መኖሩን አንስተው በጋራ በመስራትና በማልማት ጥቅም ላይ የማዋል ስራ እንዲሳካ እንሰራለን ብለዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የጋራ ትርክት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ለትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና አለው
Jan 12, 2026 64
አዲስ አበባ፤ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የጋራ ትርክት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና እንዳለው የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ብሔራዊ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በኮንፍረንሱ ታዋቂው የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ "የጋራ የወል ትርክት ግንባታ እና ፈተናዎቹ" በሚል ርዕስ የመነሻ ጽሑፍ አቅርበዋል። በመነሻ ጽሑፋቸውም፤ ኢትዮጵያዊያን ከልዩነትና ነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ በጋራ ትርክት ላይ በማተኮር ለጽኑ ሀገረ መንግሥት ግንባታ በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። አግላይና ነጣጣይ ትርክት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ፈታኝ መሆናቸውን በመጥቀስ የዜጎችን አንድነትና አብሮነት የሚያጠናክር የወል ትርክት መፍጠር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ የወል ትርክት ግንባታም በታሪክ ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ ስብራቶችን በሚያርቅ አካሄድ አብሮነትን በሚያጸኑና ሁሉንም ወገኖች በሚያቅፉ የታሪክ እውነታዎች ላይ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል። ምሁራን ታሪክን ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕዝቦች መቀራረብ እንዲውል የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ ሂደቱንም በተሻለ የሃሳብ የበላይነት በመምራትም የተሻለችና አስተሳሳሪ ትርክት የነገሰባት ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ለተሻለ የትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አብራርተዋል። በኮንፍረንሱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማን እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያዊያንን የሚያስተሳስር ገዥ ትርክት ለመገንባት በልዩ ትኩረት እየሰራ ነው
Jan 12, 2026 59
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያዊያንን የሚያስተሳስር ገዥ ትርክት ለመገንባት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) "ሀገራዊ ማንነት፣ የጋራ ትውስታዎች እና የሀገረ መንግሥት ቅቡልነት፤ የኢትዮጵያ ተሞክሮና የተያዙ አሁናዊ አቅጣጫዎች" በሚል ርዕስ የመደመር መንግሥት ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የያዛቸውን ቁልፍ አቅጣጫዎች የሚያመላክት ጽሑፍ አቅርበዋል። በመነሻ ጽሑፋቸውም፤ ኢትዮጵያ ጥንታዊት፣ የሥልጣኔ መገኛ፣ የዳበረ የሥነ-መንግሥት ልምምድ ያላት፣ የሊግ ኦፍ ኔሽን የመጀመሪያዋ አባልና የአፍሪካ ሕብረት መሥራች መሆኗን አስረድተዋል። በ1888 ዓ.ም የዓድዋ ድልም የነፃነት ተምሳሌትነትን የተጎናጸፈች፣ በቋንቋ፣ በባህልና በማንነት ስብጥር የታደለች ብትሆንም የሀገረ መንግሥት ቅቡልነት ችግር ሌላኛው ፈታኝ ገጽታዋ ሆኖ መቆየቱን ተናግረዋል። የኢትዮጵያዊያን የጋራ ማንነትና ትውስታ በንግድ፣ በኃይማኖት፣ በፍልሰትና በተፈጥሮ አደጋዎች መስተጋብር መፈጠሩንም አብራርተዋል የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ገና ያልተጠናቀቀ በመሆኑም የተረጋጋና ቅቡልነት ያለው ሀገረ መንግሥት መገንባት የሁሉንም ተሳትፎ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። ኋላቀር የፖለቲካ ባሕል፣ የተዛባ ትርክትና ጸጋዎችን በአግባቡ አለመጠቀም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ቁልፍ ማነቆ ሆነው መቆየታቸውን አንስተዋል። በዚህ መነሻነትም የመደመር መንግስት የኢትዮጵያን ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮች በዘላቂነት እልባት ለመስጠት በግልጽ አቅጣጫ በመተለም በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በዚህም ብሔራዊ መግባባትና ዕርቀ ሰላም፣ የብሔራዊነት ገዥ ትርክትና የሐሳብ ገበያ፣ የሃሳብ ፖለቲካና ኢትዮጵያ የመግባባት ዲሞክራሲ፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የጋራ ትርክት ግንባታ የሕዝብን አብሮነት የሚያጠናክር የነገ ተስፋን የሚያንጽ ወሳኝ መሣሪያ ነው
Jan 12, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክት ግንባታ ስብራትን በመጠገን የሕዝብን አብሮነት የሚያጠናክር የነገ ተስፋን የሚያንጽ ወሳኝ መሣሪያ መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ሀገር አቀፍ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የጋራ ትርክት ግንባታ የሕዝብን አብሮነትና አንድነት የሚያጠናክር የነገ ተስፋ መገንቢያ መሣሪያ ነው። ነጣጣይ ትርክት ለሀገረ መንግስት ግንባታ እንቅፋት መሆኑን በመጠቆም፤ አሰባሳቢና የጋራ ትርክት ግንባታ ግን የሀገረ መንግስት ግንባታን በጽኑ መሰረት እንደሚያንጽ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ አሰባሳቢ ትርክት ግንባታ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ስብራቶችን በመጠገን ለዜጎች አብሮነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ወሳኝ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በመደመር መንገድ በአሰባሳቢና የጋራ ትርክት ግንባታ በዜጎቿ ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ስኬታማ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የኢትጵያዊያንን ሕብረ ብሔራዊ ትስስር የሚያሰናስሉ ዘላቂ የአሰባሳቢ ትርክት ግንባታ ሥራዎችንም በስትራቴጂክ ፖሊስ ማስደገፍ ትኩረት የተሰጠው ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል። የዜጎችን የወል ትርክት ግንባታ በጽኑ መሰረት ለማነጽ በሚደረገው ጥረትም ምሁራንና ባለድርሻ አካላት ገንቢ ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አሰባሳቢና የወል ትርክት ግንባታ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያዊያንን የጋራና አሰባሳቢ ትርክት ግንባታ ላይ በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንደሚወጡ ተናግረዋል። በኮንፍረንሱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማን እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የወል ትርክት መገንባት ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወሳኝ ነው
Jan 12, 2026 85
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የወል ትርክት መገንባት ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወሳኝ መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፥ የወል ትርክት ያሉ ክፍተቶችን የሚያስታርቅ፣ በብዝኃነት ውስጥ ያሉ የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የወል ትርክትን መገንባት ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ ከፋፋይ ትርክትና እሳቤዎችን ማስወገድ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወደ ከፍታ ጉዞ መጀመሯን በማንሳት፥ ትውልዱን በጋራ ትርክት መቅረፅ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። ለዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስተሳሳሪ ትርክትን ለመገንባት በቅንጅት መሥራት አለባቸው ብለዋል። ብሔራዊ መግባባትን ለማጎልበት አሁን ትክክለኛው ጊዜ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱን በአግባቡ በመጠቀምና ሀሳብን በሰለጠነ መንገድ በማቅረብ ለውጤታማነቱ መረባረብ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ታሪክን ለመማሪያነት ብቻ መጠቀም ያስፈልጋል ያሉት አቶ መሐመድ፣ ከትናንት ጠቃሚ የሆኑ የታሪክ እሴቶችን በመውሰድ ዛሬም ተደምረን የላቀ ታሪክ መሥራት ይኖርብናል ብለዋል። በኮንፈረንሱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማን፣ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ፣ ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በሰላምና በልማት ሥራዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ የበደልነውን ህዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል
Jan 11, 2026 126
ደብረብርሃን፤ጥር 3/2018 (ኢዜአ)፡-በሰላምና ልማት ሥራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የበደልነውን ህዝብና መንግስት ለመካስ ተዘጋጅተናል ሲሉ በሰሜን ሸዋ ዞንና በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የሰላም አማራጭን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ገለጹ። በአማራ ክልል በርካታ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪን ተቀብለው ወደ ቀደመ ህይወታቸው እየተመለሱ መሆኑም ተመላክቷል። በሰሜን ሸዋ ዞንና በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ የቀድሞ ታጣቂዎች በደብረ ብርሃን የስልጠና ማዕከል ዛሬ የተሀድሶ ስልጠና መስጠት ተጀምሯል። ከተመላሾቹ መካከል ከምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የመጣው ፈለቀ ሰጤ በተሳሳተ መንገድ በመጓዝ በህዝብ ላይ ባደረሰው በደልና ጥፋት መጸጸቱን ተናግሯል። ትግሉ የህዝብን ሃብትና ንብረት በመዝረፍ ለመበልጸግ ያለመ መሆኑን በመገንዘቤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብዬ ወደሰላም ተመልሻለሁ ብሏል። ስንፈጽመው በነበረው የጥፋት ተግባር ህብረተሰቡን ከመበደል ባለፈ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው በመስተጓጎሉ ለጸጸት መዳረጉን ገልጾ፣ ከተሀድሶ ስልጠና በኋላ ህዝቡን ለመካስ እንደሚሰራ ተናግሯል። ከባሶና ወራና ወረዳ የመጣው ተስፋዬ ጌታቸው በበኩሉ፥ የህብረተሰቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ በማወክ ባደረስኩት በደል በመጸጸትና የመንግስትን ጥሪ በመቀበል ተመልሻለሁ ብለዋል። አሁንም ጫካ ቀርተው በጥፋት ተግባራቸው የቀጠሉት ትምህርት እንዲቋረጥ፣ንጹሀን እንዲገደሉ በማድረግ የሚመለስ የፖለቲካ ጥያቄ እንደሌለ ተገንዝበው ወደሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል። በቀጣይ በየአካባቢው በሚከናወኑ የሰላምና የልማት ሥራዎች ላይ ጉልህ አስተዋጾ በማድረግ የበደሉትን ህዝብና መንግስት ለመካስ ዝግጁነታቸውንም አረጋግጠዋል። ከቡልጋ ከተማ አስተዳደር የመጣው ሙሉቀን መስፍን በበኩሉ፥ ትግሉ የአማራን ህዝብ ጥያቄ የሚያስመልስ ሳይሆን የጥቂቶች ሀብት ማከማቻ እየሆነ መምጣቱን በመገንዘብ የመንግስትን የሰላም አማራጭ መቀበሉን ተናግሯል። የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ደጀኔ ልመንህ እንዳሉት፥ ሰላምን በዘላቂነት ለማጽናት ከህዝብ ጋር የተደረጉ ተደጋጋሚ ውይይቶች ውጤት እያስገኙ ናቸው። በአሁኑ ወቅት በክልሉ በርካታ ታጣቂዎች የሰላምን ጥሪ ተቀብለው ወደ ቀደመ ህይወታቸው እየተመለሱ መሆኑን ጠቁመው፣ ለተመላሾቹ የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት በፈለጉት የሙያ ዘርፍ እንዲሰማሩ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። አሁንም በጫካ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በሀይል የሚመለስ ምንም አይነት ጥያቄ እንደማይኖር በመረዳትና የጥፋት ተግባራቸውን በመተው የሰላምን አማራጭ እንዲቀበሉ አስገንዝብዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በበኩላቸው፥ በዞኑ የሰፈነው ሰላም ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ እንዲሻሻል መልካም እድል ፈጥሯል ብለዋል። መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተቀብለው የተመለሱ ወንድሞች አሁንም ሳይመለሱ በጫካ ያሉ ታጣቂዎችን መክረው ወደሰላም እንዲመለሱና የበደሉትን ህዝብ እንዲክሱ የድርሻቸውን እንዲወጡ አስገንዝበዋል። በደብረብርሃን ከተማ አስተዳደርና በዙሪያው እየሰፈነ ያለው ሰላም ለኢንዱስትሪና ለንግድ ሥራዎች መስፋፋት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የተናገሩት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት ናቸው። ወደሰላም የመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በቀጣይ በሚፈልጉት የሥራ ዘርፍ ለማሰማራት በአስተዳደሩ በኩል አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
ፖለቲካ
የአፋሕድ ምክትል ሊቀመንበር ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ የሰላም አማራጭን ተቀበሉ
Jan 12, 2026 25
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ምክትል ሊቀመንበር እና ወታደራዊ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ ከእነ ሠራዊታቸው የሰላም አማራጭን ተቀብለው ገብተዋል። ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ አፋሕድ ከአማራ ክልል መንግሥት ጋር በአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ አማካኝነት ያደረገውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የሰላም ስምምነቱን በመቀበል ከነሠራዊታቸው መግባታቸውን አሚኮ ዘግቧል። በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና በአፋሕድ መካከል ሕዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።
የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት ነው
Jan 12, 2026 21
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት መሆኑን አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። አምባሳደር ሌንጮ ባቲ በኮንፍረንሱ ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ የጋራ ትርክት መገንባት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ልዩነቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ በማምጣት መወያየትና መነጋገር እንደሚገባ ጠቁመው፤ ምክክር ማድረግ ሁነኛ አማራጭ ነው ብለዋል። አንድነትን፣ አብሮነትንና እኩልነትን የሚያጎላ ትርክት መቅረጽ እንደሚገባም ተናግረዋል። የሚያስተሳስሩ እና ዘመን ተሻጋሪ አብሮነቶችና ትስስሮችን ማጉላት የሚያስችል ትርክትን መገንባት እንደሚገባም ገልጸዋል። የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመችና የበለጸገች ኢትዮጵያን መፍጠር መሆኑንም አንስተዋል። "ሀገራዊ ማንነት፣ የጋራ ትውስታዎችና የሀገረ መንግሥት ቅቡልነት፤ የኢትዮጵያ ተሞክሮ እና የመገናኛ ብዙኃን ሚና" በሚል ርዕስ ጽሑፍ ያቀረበችው ሙኒራ አብዱልመናን መገናኛ ብዙኃን የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በማሳለጥና የዜጎችን የጋራ ማንነት በመቅረጽ ረገድ የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ተናግራለች። መገናኛ ብዙሃን ከአግላይና ነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ የወል ትርክቶችን እና እሴቶችን ማጉላት እና ማስተጋባት እንደሚገባቸው ገልጻለች። መገናኛ ብዙኃን ለብሔራዊ መግባባት ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባም ጨምራ ተናግራለች። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችም ስለ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸው ግንዛቤ ሊያድግ እንደሚገባ በመግለጽ፤ ለትውልድ የሚሻገር አስተሳሳሪ ትርክት ለመገንባት መትጋት እንደሚገባቸውም አንስታለች። በመድረኩ በኢትዮጵያ የጋራ ትርክትን ተቋማዊ ለማድረግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ሰፊ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Jan 12, 2026 42
ጋምቤላ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። የጋምቤላ ክልል የመንግስት ሰራተኞች በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ የውይይት መድረክ አካሂደዋል። በውይይት መድረኩ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ፤ በክልሉ የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት የመንግስት ሰራተኞች ተሳትፎ እና ትብብር ወሳኝ መሆኑን አንስተው በሁሉም ረገድ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠልና የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የሚነጣጥሉ እሳቤዎችን በመተው አሰባሳቢና የወል ትርክቶችን በመገንባት ረገድም የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ የሚጥሩ አካላትን በመከታተል በህግ ተጠያቂ የማድረግ፣ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥና የልማት ስራዎችን ለስኬት የማብቃት ጉዳይ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ይሰራል ብለዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) የክልሉ መንግስት የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ የልማት ስራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም የሁሉም ድጋፍና ትብብር አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በተለይም የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ አስገንዝበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን፤ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በማጠናከር ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ልንቆም ይገባል ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች መሳካት የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በጋምቤላ ክልል ለልማት የሚውል እምቅ የተፈጥሮ ሀብት መኖሩን አንስተው በጋራ በመስራትና በማልማት ጥቅም ላይ የማዋል ስራ እንዲሳካ እንሰራለን ብለዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የጋራ ትርክት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ለትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና አለው
Jan 12, 2026 64
አዲስ አበባ፤ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የጋራ ትርክት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና እንዳለው የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ብሔራዊ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በኮንፍረንሱ ታዋቂው የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ "የጋራ የወል ትርክት ግንባታ እና ፈተናዎቹ" በሚል ርዕስ የመነሻ ጽሑፍ አቅርበዋል። በመነሻ ጽሑፋቸውም፤ ኢትዮጵያዊያን ከልዩነትና ነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ በጋራ ትርክት ላይ በማተኮር ለጽኑ ሀገረ መንግሥት ግንባታ በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። አግላይና ነጣጣይ ትርክት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ፈታኝ መሆናቸውን በመጥቀስ የዜጎችን አንድነትና አብሮነት የሚያጠናክር የወል ትርክት መፍጠር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ የወል ትርክት ግንባታም በታሪክ ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ ስብራቶችን በሚያርቅ አካሄድ አብሮነትን በሚያጸኑና ሁሉንም ወገኖች በሚያቅፉ የታሪክ እውነታዎች ላይ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል። ምሁራን ታሪክን ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕዝቦች መቀራረብ እንዲውል የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ ሂደቱንም በተሻለ የሃሳብ የበላይነት በመምራትም የተሻለችና አስተሳሳሪ ትርክት የነገሰባት ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ለተሻለ የትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አብራርተዋል። በኮንፍረንሱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማን እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያዊያንን የሚያስተሳስር ገዥ ትርክት ለመገንባት በልዩ ትኩረት እየሰራ ነው
Jan 12, 2026 59
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያዊያንን የሚያስተሳስር ገዥ ትርክት ለመገንባት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) "ሀገራዊ ማንነት፣ የጋራ ትውስታዎች እና የሀገረ መንግሥት ቅቡልነት፤ የኢትዮጵያ ተሞክሮና የተያዙ አሁናዊ አቅጣጫዎች" በሚል ርዕስ የመደመር መንግሥት ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የያዛቸውን ቁልፍ አቅጣጫዎች የሚያመላክት ጽሑፍ አቅርበዋል። በመነሻ ጽሑፋቸውም፤ ኢትዮጵያ ጥንታዊት፣ የሥልጣኔ መገኛ፣ የዳበረ የሥነ-መንግሥት ልምምድ ያላት፣ የሊግ ኦፍ ኔሽን የመጀመሪያዋ አባልና የአፍሪካ ሕብረት መሥራች መሆኗን አስረድተዋል። በ1888 ዓ.ም የዓድዋ ድልም የነፃነት ተምሳሌትነትን የተጎናጸፈች፣ በቋንቋ፣ በባህልና በማንነት ስብጥር የታደለች ብትሆንም የሀገረ መንግሥት ቅቡልነት ችግር ሌላኛው ፈታኝ ገጽታዋ ሆኖ መቆየቱን ተናግረዋል። የኢትዮጵያዊያን የጋራ ማንነትና ትውስታ በንግድ፣ በኃይማኖት፣ በፍልሰትና በተፈጥሮ አደጋዎች መስተጋብር መፈጠሩንም አብራርተዋል የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ገና ያልተጠናቀቀ በመሆኑም የተረጋጋና ቅቡልነት ያለው ሀገረ መንግሥት መገንባት የሁሉንም ተሳትፎ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። ኋላቀር የፖለቲካ ባሕል፣ የተዛባ ትርክትና ጸጋዎችን በአግባቡ አለመጠቀም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ቁልፍ ማነቆ ሆነው መቆየታቸውን አንስተዋል። በዚህ መነሻነትም የመደመር መንግስት የኢትዮጵያን ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮች በዘላቂነት እልባት ለመስጠት በግልጽ አቅጣጫ በመተለም በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በዚህም ብሔራዊ መግባባትና ዕርቀ ሰላም፣ የብሔራዊነት ገዥ ትርክትና የሐሳብ ገበያ፣ የሃሳብ ፖለቲካና ኢትዮጵያ የመግባባት ዲሞክራሲ፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የጋራ ትርክት ግንባታ የሕዝብን አብሮነት የሚያጠናክር የነገ ተስፋን የሚያንጽ ወሳኝ መሣሪያ ነው
Jan 12, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክት ግንባታ ስብራትን በመጠገን የሕዝብን አብሮነት የሚያጠናክር የነገ ተስፋን የሚያንጽ ወሳኝ መሣሪያ መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ሀገር አቀፍ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የጋራ ትርክት ግንባታ የሕዝብን አብሮነትና አንድነት የሚያጠናክር የነገ ተስፋ መገንቢያ መሣሪያ ነው። ነጣጣይ ትርክት ለሀገረ መንግስት ግንባታ እንቅፋት መሆኑን በመጠቆም፤ አሰባሳቢና የጋራ ትርክት ግንባታ ግን የሀገረ መንግስት ግንባታን በጽኑ መሰረት እንደሚያንጽ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ አሰባሳቢ ትርክት ግንባታ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ስብራቶችን በመጠገን ለዜጎች አብሮነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ወሳኝ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በመደመር መንገድ በአሰባሳቢና የጋራ ትርክት ግንባታ በዜጎቿ ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ስኬታማ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የኢትጵያዊያንን ሕብረ ብሔራዊ ትስስር የሚያሰናስሉ ዘላቂ የአሰባሳቢ ትርክት ግንባታ ሥራዎችንም በስትራቴጂክ ፖሊስ ማስደገፍ ትኩረት የተሰጠው ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል። የዜጎችን የወል ትርክት ግንባታ በጽኑ መሰረት ለማነጽ በሚደረገው ጥረትም ምሁራንና ባለድርሻ አካላት ገንቢ ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አሰባሳቢና የወል ትርክት ግንባታ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያዊያንን የጋራና አሰባሳቢ ትርክት ግንባታ ላይ በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንደሚወጡ ተናግረዋል። በኮንፍረንሱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማን እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የወል ትርክት መገንባት ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወሳኝ ነው
Jan 12, 2026 85
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የወል ትርክት መገንባት ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወሳኝ መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፥ የወል ትርክት ያሉ ክፍተቶችን የሚያስታርቅ፣ በብዝኃነት ውስጥ ያሉ የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የወል ትርክትን መገንባት ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ ከፋፋይ ትርክትና እሳቤዎችን ማስወገድ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወደ ከፍታ ጉዞ መጀመሯን በማንሳት፥ ትውልዱን በጋራ ትርክት መቅረፅ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። ለዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስተሳሳሪ ትርክትን ለመገንባት በቅንጅት መሥራት አለባቸው ብለዋል። ብሔራዊ መግባባትን ለማጎልበት አሁን ትክክለኛው ጊዜ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱን በአግባቡ በመጠቀምና ሀሳብን በሰለጠነ መንገድ በማቅረብ ለውጤታማነቱ መረባረብ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ታሪክን ለመማሪያነት ብቻ መጠቀም ያስፈልጋል ያሉት አቶ መሐመድ፣ ከትናንት ጠቃሚ የሆኑ የታሪክ እሴቶችን በመውሰድ ዛሬም ተደምረን የላቀ ታሪክ መሥራት ይኖርብናል ብለዋል። በኮንፈረንሱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማን፣ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ፣ ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በሰላምና በልማት ሥራዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ የበደልነውን ህዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል
Jan 11, 2026 126
ደብረብርሃን፤ጥር 3/2018 (ኢዜአ)፡-በሰላምና ልማት ሥራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የበደልነውን ህዝብና መንግስት ለመካስ ተዘጋጅተናል ሲሉ በሰሜን ሸዋ ዞንና በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የሰላም አማራጭን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ገለጹ። በአማራ ክልል በርካታ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪን ተቀብለው ወደ ቀደመ ህይወታቸው እየተመለሱ መሆኑም ተመላክቷል። በሰሜን ሸዋ ዞንና በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ የቀድሞ ታጣቂዎች በደብረ ብርሃን የስልጠና ማዕከል ዛሬ የተሀድሶ ስልጠና መስጠት ተጀምሯል። ከተመላሾቹ መካከል ከምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የመጣው ፈለቀ ሰጤ በተሳሳተ መንገድ በመጓዝ በህዝብ ላይ ባደረሰው በደልና ጥፋት መጸጸቱን ተናግሯል። ትግሉ የህዝብን ሃብትና ንብረት በመዝረፍ ለመበልጸግ ያለመ መሆኑን በመገንዘቤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብዬ ወደሰላም ተመልሻለሁ ብሏል። ስንፈጽመው በነበረው የጥፋት ተግባር ህብረተሰቡን ከመበደል ባለፈ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው በመስተጓጎሉ ለጸጸት መዳረጉን ገልጾ፣ ከተሀድሶ ስልጠና በኋላ ህዝቡን ለመካስ እንደሚሰራ ተናግሯል። ከባሶና ወራና ወረዳ የመጣው ተስፋዬ ጌታቸው በበኩሉ፥ የህብረተሰቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ በማወክ ባደረስኩት በደል በመጸጸትና የመንግስትን ጥሪ በመቀበል ተመልሻለሁ ብለዋል። አሁንም ጫካ ቀርተው በጥፋት ተግባራቸው የቀጠሉት ትምህርት እንዲቋረጥ፣ንጹሀን እንዲገደሉ በማድረግ የሚመለስ የፖለቲካ ጥያቄ እንደሌለ ተገንዝበው ወደሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል። በቀጣይ በየአካባቢው በሚከናወኑ የሰላምና የልማት ሥራዎች ላይ ጉልህ አስተዋጾ በማድረግ የበደሉትን ህዝብና መንግስት ለመካስ ዝግጁነታቸውንም አረጋግጠዋል። ከቡልጋ ከተማ አስተዳደር የመጣው ሙሉቀን መስፍን በበኩሉ፥ ትግሉ የአማራን ህዝብ ጥያቄ የሚያስመልስ ሳይሆን የጥቂቶች ሀብት ማከማቻ እየሆነ መምጣቱን በመገንዘብ የመንግስትን የሰላም አማራጭ መቀበሉን ተናግሯል። የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ደጀኔ ልመንህ እንዳሉት፥ ሰላምን በዘላቂነት ለማጽናት ከህዝብ ጋር የተደረጉ ተደጋጋሚ ውይይቶች ውጤት እያስገኙ ናቸው። በአሁኑ ወቅት በክልሉ በርካታ ታጣቂዎች የሰላምን ጥሪ ተቀብለው ወደ ቀደመ ህይወታቸው እየተመለሱ መሆኑን ጠቁመው፣ ለተመላሾቹ የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት በፈለጉት የሙያ ዘርፍ እንዲሰማሩ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። አሁንም በጫካ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በሀይል የሚመለስ ምንም አይነት ጥያቄ እንደማይኖር በመረዳትና የጥፋት ተግባራቸውን በመተው የሰላምን አማራጭ እንዲቀበሉ አስገንዝብዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በበኩላቸው፥ በዞኑ የሰፈነው ሰላም ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ እንዲሻሻል መልካም እድል ፈጥሯል ብለዋል። መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተቀብለው የተመለሱ ወንድሞች አሁንም ሳይመለሱ በጫካ ያሉ ታጣቂዎችን መክረው ወደሰላም እንዲመለሱና የበደሉትን ህዝብ እንዲክሱ የድርሻቸውን እንዲወጡ አስገንዝበዋል። በደብረብርሃን ከተማ አስተዳደርና በዙሪያው እየሰፈነ ያለው ሰላም ለኢንዱስትሪና ለንግድ ሥራዎች መስፋፋት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የተናገሩት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት ናቸው። ወደሰላም የመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በቀጣይ በሚፈልጉት የሥራ ዘርፍ ለማሰማራት በአስተዳደሩ በኩል አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
ማህበራዊ
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለልማት ሥራዎች ስኬታማነት የሚያበረክቱትን አስተዋጾ ማጠናከር አለባቸው
Jan 12, 2026 39
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፡-የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለሀገራዊ የልማት ሥራዎች ስኬታማነት በቅንጅት የሚያበረክቱትን አስተዋጾ ማጠናከር እንዳለባቸው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስታወቀ። 14ኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን እና የፌደራልና የክልል ባለድርሻ አካላት የጋራ ጉባኤ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል። "የመንግስትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ትብብርና ቅንጅት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው መድረክ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ እንደገለጹት፣ ድርጅቶቹ ለሀገራዊ ልማትና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያላቸው የላቀ ሚና ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። በተለይ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ሥራዎች ስኬታማነት እያበረከቱት ያለውን አስተዋጽኦ አጠናክረው ማስቀጠል አንዳለባቸው ጠቅሰው፣ ለዚህም ከመንግስት ጋር ይበልጥ ተቀራርበው እንዲሰሩ ከማድረግ ባለፈ አሰራሮችን የማዘመን ሥራ ይሰራል ብለዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ራሳቸውን በራሳቸው የሚያስተዳድሩበት ጠንካራ ስርአት ለመዘርጋት ሲሰራ መቆየቱንና በዚህም ውጤት መመዝገቡን አመልክተዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በክልሉ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ የልማት ሥራዎችና እድገት ስኬታማነት የሚያደርጉት አስተዋጾ የላቀ መሆኑን አንስተዋል። ድርጅቶቹ በክልሉ ሚናቸውን በተቀናጀ መንገድ እንዲወጡም የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀትና ምክር ቤት በማቋቋም በተቀናጀ መንገድ እንዲንቀሳቀሱ የማድረግ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። በክልሉ የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎቶች በማገዝ ረገድ እያበረከቱት ያለው አስተዋጾ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ያሉት አቶ ገብረመስቀል ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ይሰራል ብለዋል። ድርጅቶቹ በክልሉ የበጎ ፍቃደኝነት እና የበጎ አድራጊነት ባህልን በማጎልበትና በማስረጽ በልማትና በዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲኖራቸው በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በክልሉ ከ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ያስመዘገቡ 132 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንዳሉ ያነሱት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ ናቸው። ድርጅቶቹ ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን በተለያዩ የልማት ሥራዎች ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን አንስተዋል። ይህን አበርክቶ ለማጠናከር የትብብርና የክትትል ስራው ልዩ ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸው፣ የድርጅቶቹ የአጋርነት ሚና እያደገ መምጣቱንም አስታውቀዋል። በመድረኩ ከፌደራልና ከክልሎች የመጡ ባለድርሻ አካላት፣ የፍትህና የፋይናንስ ቢሮዎች ተወካዮች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተሳትፈዋል።
በአዳማ ከተማ ከ40 ሺህ በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር ተጠቃሚ ሆነዋል
Jan 12, 2026 41
አዳማ፤ ጥር4/2018 (ኢዜአ)፡- በአዳማ ከተማ ከ40 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተጠቃሚ ያደረገ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር ተጠናከሮ መቀጠሉን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ጽህፈት ቤት ገለጸ። የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ደረጀ ተስፋዬ ለኢዜአ እንዳሉት በከተማ አስተዳደሩ በ116 ትምህርት ቤቶች የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው። መርሃ ግብሩም በከተማ አስተዳደሩ ቡሳ ጎኖፋ፣ በህብረተሰቡ፣ በባለሀብቶች እና በተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። በአጠቃላይ በትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብሩ ከ40 ሺህ በላይ የቅድመ መደበኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተዋል። የትምህርት ቤት የምገባ መርሃ ግብሩ፣ የተማሪዎች መጠነ ማቋረጥ መቀነስና የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል ማስቻሉን ጠቅሰዋል። ከዚህ አንጻር በከተማ አስተዳደሩ በ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መካከል 93 በመቶ በላይ ወደ ቀጣዩ ክፍል ማለፋቸውን ተናግረዋል። የአዳማ ከተማ አስተዳደር ቡሳ ጎኖፋ ኃላፊ አቶ ዋዶ አብዱልከሪም በበኩላቸው ቡሳ ጎኖፋ ለትምህርት ቤት ምገባ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለተግባራዊነቱም ከህብረተሰቡና ከአጋር አካላት የምግብ እህልና ገንዘብ በማሰባሳብ መርሃ ግብሩን ማሳካት መቻሉን ጠቁመዋል። በዚህም 42 ሺህ 456 ተማሪዎች ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰው በቀጣይም ተግባሩን ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል።
በክልሉ የጤና አገልግሎትን በማዘመን የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቷል
Jan 12, 2026 44
ወራቤ ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጤና አገልግሎትን ዲጂታላይዝ በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማጎልበት ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በክልሉ በጤናው ስርዓት ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመና ለዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች የተዘጋጀ ስልጠና ዛሬ በወራቤ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል። "ጠንካራ የአመራር ስርዓት ግንባታ ለውጤታማ የጤና ስርዓት" በሚል መሪ ሀሳብ እየተሰጠ ያለው ስልጠና ከዛሬ ጀምሮ ለስምንት ቀናት እንደሚቆይ ታውቋል። የቢሮው ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ በጤናው ዘርፍ ጠንካራ የአመራር ስርዓት በመፍጠር የላቀ እመርታ ለማስመዝገብ እንዲቻል ታስቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በክልሉ በጤናው ሥርዓት ላይ የተስተዋሉና በጥናት የተለዩ ችግሮችን በማረም ቀልጣፋና ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የጤና አገልግሎት ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማገዝ አገልግሎቱን ከማዘመን ባለፈ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። ወቅቱ የደረሰበትን ደረጃ የሚመጥን የጤና አገልግሎት ለማህበረሰቡ በፍትሀዊነት ተደራሽ ለማድረግ ባለፉት ስድስት ወራት ሁለት አጠቃላይ ሆስፒታሎችን ጨምሮ በአምስት የጤና ተቋማት ከወረቀት ነፃ የሆነ የሕክምና አገልግሎት ተደራሽ መደረጉንም ነው የገለጹት። ዛሬ የተጀመረው ስልጠናም የጤና አገልግሎት ስርዓቱን በዲጂታላይዝ በማገዝ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ያግዛል ብለዋል። ከክልሉ መንግስትና ከጤና ሚኒስቴር ድጋፍ በተጨማሪ ማህበረሰቡን በማስተባበር በጤና ተቋማት ግንባታ፣ በመድኃኒት አቅርቦትና በህክምና ግብዓቶችን ማሟላት ላይ የተሰራው ስራ ውጤት እየተመዘገበበት መሆኑንም አቶ ሳሙኤል አክለዋል፡፡ ለዚህም በ71 ጤና ተቋማት የአልትራሳውንድ ሕክምና አገልግሎት እንዲሰጥ መደረጉንና በክልሉ የኮምፕሬሄንሲቭ ጤና ኬላዎችን ተደራሽነት ለማስፋት እየተሰራ ያለውን ስራ በማሳያነት ጠቅሰዋል። በክልሉ ጤናው የተጠበቀ ማህበረሰብን ለመፍጠር የተጀመረውን ሥራ ለማጠናከር አመራሩ ማህበረሰቡን በማስተባበርና በአካባቢው የሚገኝን ሀብት በመጠቀም በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት እንዲያስመዘግብ ስልጠናው አጋዥ መሆኑም አመልክተዋል ለተከታታይ 8 ቀናት በሚሰጠው ስልጠና ላይ ከተለያዩ የወረዳ መዋቅር የተውጣጡ ከ200 በላይ የጤና ዘርፍ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
መንግስት ለባህል ጥበባትና ስፖርት ዘርፉ በሠጠው ልዩ ትኩረት ስኬታማ ስራዎችን መስራት ተችሏል- ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ
Jan 12, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦መንግስት ለባህል ጥበባትና ስፖርት ዘርፉ በሠጠው ልዩ ትኩረት ስኬታማ ስራዎችን መስራት ተችሏል ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለጹ። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር "የባህል፣ ጥበባትና ስፖርት ዕምርታ ለኢትዮጵያ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሴክተር ጉባኤ እያካሄደ ነው። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በጉባኤው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በባህል ጥበባትና ስፖርት ዘርፍ ባለፉት 6 ወራት የላቀ ስኬት መከናወኑን ገልፀዋል። መንግስት ለስፖርት ልማት በሰጠው ልዩ ትኩረት ውድድሮችን በማስቀጠል፤ ነባሩን የስፖርት ፖሊሲ በማሻሻል ማፀደቅ እንዲሁም በዓለምአቀፍ መድረክ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደተቻለ አንስተዋል። አጠቃላይ በሀገሪቱ ጥርጊያ ሜዳዎችን ጨምሮ 43 ሺህ 335 የይዞታ ማረጋገጫ ያላቸው ስፍራዎች ያሉ መሆኑን የገለጹ ሲሆን 15 ሺህ 796 ሜዳዎች ባለፉት 8 ዓመታት ብቻ የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ ያገኙ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ከጥበባት ዘርፍ አንፃር የኢትዮጵያን መልክ አጉልተው የሚያሳዩ የጥበብ ስራዎች የተሰሩበት፤ ታላላቅ ኮንፈረንሶችና መድረኮች የተካሄዱበት መሆኑም ተገልጿል። የህዝብ እና የአደባባይ በዓላትን በመጠቀም የህዝብ ለህዝብ ትስስር የተፈጠረበት፤ የቋንቋና የበዓላት ፕሮፋይል የተሰነደበት፣ የጥናትና ምርምር ስራዎች ከባህልና ቋንቋ ዘርፍ አንፃር መከናወናቸውን ተናግረዋል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ የሚያጸኑ አስደማሚ የልማት ስኬቶች እየተመዘገቡ ነው
Jan 12, 2026 40
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ የሚያጸኑ አስደማሚ የልማት ስኬቶች መመዝገባቸውን የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የበጀት ዓመቱን ያለፉት ስድስት ወራት የልማት አፈፃጸም አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፥ 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዓመት ነው ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራትም የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያጸኑ አስደማሚ የልማት ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህም በብዝኅ የኢኮኖሚ ዘርፍ በ2030 ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት የሚያደርጉ የልማት ስኬቶች እየተመዘገቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት የጉባ ብስራት ፕሮጀክቶች ጅማሮም ኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ጀምራ ማጠናቀቅ እንደምትችል የሚያሳዩ መሆናቸውን አብራርተዋል። ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካና የዓለም የአየር ትራንስፖርት ፋና ወጊ በማድረግ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማሪፊያ ግንባታ መጀመር የንግድ ትስስርን ለማሳለጥ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው በአብነት ጠቅሰዋል። የመደመር መንግሥት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያም በሁሉም መስኮች ችግሮችን በማረም የኢትዮጵያን ዕድገት የሚያሳልጥ ውጤት መመዝገቡን አብራርተዋል። በዚህም በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና ዲጂታል ብዝኅ የኢኮኖሚ መስኮች እመርታዊ ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት እሳቤ በግብርና መስክ በበጋ መስኖ ስንዴ፣ በኩታ ገጠምና በሌማት ትሩፋት የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት በማረጋገጥ ተመጽዋችነትን የሚገታ የምርት ውጤት እየተገኘ መሆኑን አንስተዋል። የጉባ ብስራት ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅም ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ ጠቅሰዋል። ከተሞችን የብልጽግና ማዕከል ለማድረግ በአዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማትም በበርካታ ከተሞች በስፋት እየተሰራበት መሆኑን ገልጸዋል። በዲፕሎማሲ መስክም በአሕጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረኮች የኢትዮጵያ ተሳትፎም ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ የአፍሪካ ድምጽ መሆን ያስቻለ ስኬት መመዝገቡን ተናግረዋል። በመንግስትና ሕዝብ መካከል የተደረጉ መድረኮችም ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የልማት ስኬት ዕውቅና የተሰጠበት መሆኑን አብራርተዋል። በዚህ ዓመት የሚካሄዱት የሀገራዊ ምክክርና ሀገራዊ ምርጫ ዐበይትና ወሳኝ ሁነቶችን በአሳታፊነት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ በስኬት ለማስኬድም መንግስት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ከክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት 33ሺህ 700 ቶን የቡና፣ ሻይ እና ቅመማቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል
Jan 12, 2026 51
ቦንጋ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል 33ሺህ 700 ቶን የቡና፣ ሻይ እና ቅመማቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡ ተመለከተ። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ የሺዋስ ዓለሙ፤ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትንና ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል። በተለይም በግብርናው ዘርፍ በዋና ዋና ሰብሎች እንዲሁም በቡና፣ ሻይ እና ቅመማቅመም ምርቶች ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በዚህም መሰረት በክልሉ በዋና ዋና ሰብሎች 384 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት ከ20 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት 33 ሺህ 700 ቶን የቡና፣ ሻይ እና ቅመማቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን ጠቁመው ከቀረበው ውስጥ 13ሺህ ቶኑ ቡና፣ 2ሺህ 700 ቶኑ ሻይ እና 18 ሺህ ቶኑ ቅመማቅመም መሆኑን አመልክተዋል። በሌላ በኩል በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ255 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መቅረቡንም ጠቁመዋል። በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ አገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች ለተሰማሩ 52 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል። በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርም በርካቶች ተሰማርተው ስኬታማ መሆናቸውንና ለሌሎችም ጭምር የስራ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል። የውሃ፣ የመስኖ፣ የመንገድና ድልድዮችን፣ እንዲሁም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ መሰረተ ልማቶች መከናወናቸውን ተናግረዋል። በተለይም በከተሞች ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል አገልግሎት በመስጠት በኩል መልካም ጅምሮች መኖራቸውን አንስተው በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በክልሉ ሕገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ገበያን የማረጋጋት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jan 12, 2026 77
ሚዛን አማን፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ሕገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ገበያን ለማረጋጋት የተሰራው ሥራ ውጤታማ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ኃላፊ አቶ ታሪኩ አካሉ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሕገወጥ ንግድና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ የገበያ ዋጋን በማናር በዜጎችና በሀገር ላይ ጉዳት ያደርሳል። ይህን ለማስቅረትም በክልሉ በህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ላይ የሚሳተፉ አካላትን ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ የመከላከል ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት በምርቶች ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉና በሕገ ወጥ የነዳጅ ግብይትና መሰል ተግባራት ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎችን በመከታተል እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል። እንደኃላፊው ገለጻ፤ በገንዘብ ከተቀጡት ነጋዴዎች መካከል 1ሺህ 670 የሚሆኑት ለመንግስት ሠራተኞች የተደረገን የደመወዝ ማሻሻያን ተከትሎ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረጋቸው እርምጃ የተወሰደባቸው ናቸው። በቀጣይም የተጋነነ የዋጋ ጭማሪና የምርት ስወራ እንዳይኖር በመከላከል ገበያን ለማረጋጋት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አመልክተዋል። ባለፉት ስድስት ወራት ገበያን ለማረጋጋት የተሰሩ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የገለጹት ሃላፊው፣ ህጋዊ የግብይት ስርዓቱን ለማጠናከርም ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። ከሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ወይንሸት ዘውዴ፤ መንግሥት በንግድ እንቅስቃሴው ላይ የሚፈጸሙ ህገወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ለሸማቹ መብት መከበር ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። አንዳንድ ነጋዴዎች በሕገ ወጥ መንገድ ለመክበር የሚያደርጉት ጥረት ሕዝብና ሀገር ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚፈጥር ገልጸው፣ በመንግስት ህገወጥነትን ለመከላከል ለሚሰሩ ሥራዎች በአቅማቸው ለመደገፍ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
በአፋር ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ3 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ
Jan 12, 2026 46
ሰመራ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ3 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኀላፊ አቶ አወል አብዱ፤ የበጀት ዓመቱን የስድስት ወራት የገቢ አሰበሰብ ሂደቱን አስመልክተው ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። አቶ አወል በመግለጫቸው፤በበጀት ዓመቱ በስድስት ወራት ውስጥ 4 ቢሊዮን 78 ሚሊዮን 630 ሺህ ለመሰብሰብ ታቅዶ 3 ቢሊየን 998 ሚሊዮን 779 ሺህ ብር መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል። ገቢው የተሰበሰበው ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ ታክሶችና ከሌሎች የገቢ አርዕስቶች መሆናቸውንም ገልጸዋል። በግብር አሰባሰቡ የእቅዱን 98 በመቶ ማከናወን መቻሉን ገልፀው በቀጣይም የገቢ አሰባበሰብ ሂደቱን በማዘመን የክልሉን ልማት ለማሳካት ርብርብ እንደሚደረግ ተናግረዋል። የገቢ አፈጻጸሙ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫና የ50 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ሃላፊው አስረድተዋል። በክልሉ ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ የሚያስችል ከክልል እስከ ቀበሌ ድረስ በተሰሩ የንቅናቄና የግንዛቤ ማሳደግ ስራዎች ግብርን በጊዜ የመክፈል ሁኔታው እየተሻሻለ መምጣቱን ገልፀዋል። በተለይም የግብር አሰባሰቡን ዲጂታላይዝ በማድረግ ግብር ከፋዩ በቀላሉ መስተናገድ እንዲችል በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዘርፉ የተሻሉ አሰራሮችን በመዘርጋትና ህገ ወጥ ግለሰቦችን ወደ ህጋዊነት የማምጣት ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመው፤ ወደ ትክክለኛው መንገድ መምጣት ባልቻሉት ላይ ደግሞ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም አቶ አወል ገልጸዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በአስተዳደሩ ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት የሚያሳልጥ የቴክኖሎጂ አሰራር አቅም ተገንብቷል
Jan 12, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት የሚያሳልጥ የቴክኖሎጂ አሰራር አቅም መገንባቱን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ 23 ወረዳዎች በኃይል መቆራረጥ የሚፈጠርን የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተት ምላሽ የሚሰጥ የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። በዚሁ ጊዜ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ፤ የመዲናዋን ነዋሪዎች የተቋማት የአገልግሎት ፍላጎት እርካታ የሚያረጋግጥ ዘመናዊ አሰራር እየተዘረጋ ነው ብለዋል። በዚህም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፈጠረው ዘመናዊ የቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓት አቅም ለተገልጋዮች የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማሳለጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በወረዳዎች የተገነባው የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክትም በኃይል መቆራረጥ ምክንያት የሚፈጠርን የአገልግሎት ክፍተት ምላሽ በመስጠት የደንበኛ እርካታን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በተለይም በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ወቅት የኤሌክትሪክ ኃይል ሲቋረጥ ለሚፈጠሩ የአገልግሎት ክፍተቶች አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ለደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚረዳ አስረድተዋል። በቀጣይም የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች በአስተማማኝ የኃይል አቅርቦትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ አሰራር የማስቀጠል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አንስተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ፤ የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክቱ የወሳኝ ኩነት አገልግሎቶችን ለማሳለጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል ብለዋል። በቀጣይም አገልግሎት በሚበዛባቸው ወረዳዎች የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክቶችን በማስፋት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲያገኙ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል። የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ እሸቱ ለማ (ዶ/ር)፤ የፀሐይ ኃይል ፕሮጀክቱ በኃይል መቆራረጥ ምክንያት የሚፈጥርን የአገልግሎት ክፍተት አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንደሚረዳ ተናግረዋል።
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተከናወኑ ተግባራት ሀገር ወደተሻለ ከፍታ እንድታመራ መሰረት ጥለዋል
Jan 11, 2026 144
ወልቂጤ፤ ጥር 3/2018 (ኢዜአ)፡-በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የተከናወኑ ተግባራት ሀገሪቱ ወደተሻለ ከፍታ እንድታመራ መሰረት የጣሉ መሆናቸውን የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። ስትራቴጂው በቅርቡ ይፋ የተደረገውን ዲጂታል 2030 ትግበራን ለማሳካት ትልቅ ግብዓት እንደሚሆንም ምሁራኑ ጠቁመዋል። መንግስት የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ በየዘርፉ የጀመራቸውን ሥራዎች ይበልጥ ለማዘመንና ለማሳለጥ በቅርቡ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ምሁራኑ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተተገበሩ ቴክኖሎጂዎች ሀገሪቱ ወደተሻለ ከፍታ እንድታመራ መሰረት የጣሉ ናቸው። ዲጂታል ቴክኖሎጂው በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርትና በፋይናንስ ዘርፎች ያመጣው ተጨባጭ ለውጥና ያስገኘው ጥቅም እያደገ መሆኑን የተናገሩት በዩኒቨርሲቲው የሶፍት ዌር ኢንጂነሪንግ መምህር በላይ አለምነህ ናቸው። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬቶች በዘርፉ ልምድና ተሞክሮ የተቀሰመበት መሆኑን ገልጸው፣ በስትራቴጂው በተዘረጉ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶች በተለያዩ ተቋማት ከወረቀት ነጻ የሆነ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተናግረዋል። በዩኒቨርሲቲውም የትምህርት መርሃ ግብሮችና በሥራ ክፍሎች የመረጃ ልውውጥ ሥራው ከወረቀት ነጻ በሆነ መንገድ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዞ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪ የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በመደረጉ ተማሪዎች ጊዜና ቦታ ሳይገድባቸው ትምህርታቸውን በኦንላይን መከታተል መቻላቸውን ጠቁመዋል። ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ ተቋማት እና ግለሰቦች ጋር የሚያደርገው ግንኙነትና የተማሪዎች ውጤትም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደራሽ መደረጋቸውንም ነው ያመለከቱት። የመማር ማስተማር ሂደቱን በማዘመንና የፈተና አሰጣጥ ሥርአቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የፈተናን ደህንነት ለማስጠበቅ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም አስረድተዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራት በቅርቡ ይፋ ለተደረገው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ መሰረትና ግብአት መሆናቸውን ተናግረዋል። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኔትዎርኪንግ ሳይበር ደህንነት መምህር ወንድወሰን ዝና በበኩላቸው ለተማሪዎች በሳይበር መረጃ ደህንነት አጠባበቅ ላይ በተግባር የተደገፈ ትምህርት ለመስጠትና በቂ ዕውቀት ለማስጨበጥ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 አበርክቶ ላቅ ያለ መሆኑን ተናግረዋል። በየደረጃው ለትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ይበልጥ መረጋገጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸው፣ "ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠል በዲጂታል ቴክኖሎጂ ያሉ አማራጮችን በአግባቡ ልንጠቀምባቸው ይገባል" ብለዋል። ስትራቴጂው ዜጎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ አማራጮች ታግዘው ባሉበት ቦታ ትምህርታቸውን መከታተል የሚችሉበት ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ጠቁመዋል። እንደ መምህሩ ገለጻ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተግባራዊ መሆን እንደሀገር ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ከመከላከል ባለፈ የተለያዩ ማጭበርበሮችን ለማስቀረትም እያገዘ ነው። ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ አካታችና ተደራሽ እንዲሆን በማድረግ በሁሉም ዘርፍ ተግባራትና የሚሰጡ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ የታገዙና ቀልጣፋ እንዲሆኑ የተጀመሩ ሥራዎች መጠናከር እንዳለባቸውም መምህሩ ገልጸዋል።
በከተማው ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች የዲጂታል እውቀት የማሳደግ ስራ ይከናወናል
Jan 11, 2026 124
ጎንደር ፤ጥር 3/2018(ኢዜአ)፡- በስራ ፈጠራ የሚሰማሩ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ለማጎልበት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጎንደር ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። የጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና "ኦርቢት ኢኖቬሽን ሀብ" የተባለ ድርጅት በጋራ በመሆን በስራ ፈጠራ ክህሎት ላሰለጠኗቸው 45 ወጣቶች ዛሬ የማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል። የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ ደብሬ የኋላ ለሰልጣኞቹ እንደገለጹት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ለማሳካት ልዩ የስራ ፈጠራ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች ተሳትፎ ማሳደግ ይገባል። የከተማ አስተዳደሩ ልዩ የስራ ፈጠራ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች ተቋማዊ የአሰራር ስርአቶችን በመዘርጋት ውጤታማና እንዲሆኑ ሁለተናዊ ድጋፍ በማድረግ ሃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል፡፡ የዲጂታል ቴክኖሎጂ በሀገራችን ለተዘመገቡ ኢኮኖሚያዊ እድገቶች አዎንታዊ ሚና እንደነበረው ጠቁመው የሰራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በከተማው በማደራጀት ተሰጥዋቸውን ለሀገር ልማትና እድገት የሚያውሉበት ምቹ አውድ እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ የጎንደር ከተማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተስፋሁን መኮንን እንደገለጹት የስራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች የዲጂታል ክህሎትና እውቀታቸው እንዲዳብር ኮሌጁ ተገቢውን የሙያ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል፡፡ የስራ ፈጠራ ሃሳብ ተወዳዳሪነትን፣ ብቃትንና ዘመኑን የዋጀ መሆን እንዳለበት ጠቁመው ለስልጠናው የተመረጡ ወጣቶችም መስፈርቱን ያሟሉ እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡ "የኦርቢት ኢኖቬሽን ሀብ" የኮሚኒቲ ዴቨሎፕመንት ፕሮግራም ማኔጀር ቅኔል ሃይሉ በበኩላቸው በሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች የስራ ፈጣሪ ወጣቶችን ራእይ ለማሳካት የዲጂታል ክህሎት ስልጠና የሚያገኙበት አሰራርን በመዘርጋት አየተተገበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ድርጅቱ ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር በመተባበር በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በትግራይና በደቡብ ክልሎቸ በ6 ዙር የስራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በማወዳደር የቴክኖሎጂ ስልጠና እንዲያገኙ እየደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በጎንደር ከተማም 218 የስራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በማወዳደር ከዚህ ውስጥ መመዘኛውን ያለፉ 45 ወጣቶች ለሶስት ተከታታይ ወራት የንድፈ ሃሳብና የተግባር ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ የሚገቡበትን ሁኔታ ማመቻቸቱን አስረድተዋል፡፡ ከሰልጣኞቹ መካከል የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር አዲሱ ወርቄ ስልጠናው በዲጂታል አለም ውስጥ የስራ ፈጠራ ሃሳቦቻችንን አንዴት ማሳካት እንደምንችል እውቀትና ክህሎት መጨበጥ እንድንችል አግዞናል ብለዋል፡፡ የሳይካትሪስት ባለሙያ የሆነችው ቤተልሄም ጌታቸው በበኩሏ የስራ ፈጠራ ሃሳቦቼን እንዴት ወደ መሬት ማውረድና ገበያ ላይ ማውጣት አንደምችል ስልጠናው የተሟላ እውቀትና ግንዛቤ ፈጥሮልኛል ብላለች። በስነ ስርአቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ ስልጠናውን የተከታተሉ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ተሳታፊ ናቸው፡፡
ስፖርት
በኤፍኤ ካፕ ሊቨርፑል ከባርንስሌይ ጋር ይጫወታል
Jan 12, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ኤፍኤ ካፕ የሶስተኛ ዙር መርሃ ግብር ሊቨርፑል ከባርንስሌይ ጋር ዛሬ ጨዋታውን ያደርጋል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት ከ45 ላይ በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም ይካሄዳል። ሊቨርፑል የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን ለስምንት ጊዜ በማንሳት ስኬታማ ከሚባሉ ክለቦች አንዱ ነው። በእንግሊዝ ሶስተኛ የሊግ የውድድር እርከን (ሊግ ዋን) የሚገኘው ባርንስሌይ አንድ ጊዜ ውድድሩን አሸንፏል። ሁለቱ ክለቦች በኤፍኤ ካፕ ሲገናኙ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ነው። እ.አ.አ 1985 ለመጀመሪያ ጊዜ ተገናኝተው ሊቨርፑል 4 ለ 1 አሸንፏል። እ.አ.አ በ2008 16 ውስጥ ባደረጉት ጨዋታ ባርንስሌይ ሊቨርፑልን ሳይጠበቅ 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ ገብቷል። ክለቦቹ ከ18 ዓመታት በኋላ በመድረኩ ይገናኛሉ። ሊቨርፑል ጨዋታውን የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት አግኝቷል። የኤፍኤ ካፕ የሶስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ዛሬ አራተኛ ቀኑን ያስቆጠረ ሲሆን ነገ ይጠናቀቃል። 155 ዓመታትን ያስቆጠረው ኤፍኤ ካፕ የዓለም አንጋፋው የክለቦች ውድድር ነው።
ማንችስተር ዩናይትድ ከኤፍኤ ካፕ ውድድር ተሰናበተ
Jan 11, 2026 112
አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ኤፍኤ ካፕ የሶስተኛ ዙር መርሃ ግብር ብራይተን ማንችስተር ዩናይትድን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በኦልድትራፎርድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ብራጃን ግሩዳ እና ዳኒ ዌልቤክ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ቤንጃሚን ሼስኮ ለዩናይትድ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። የማንችስተር ዩናይትዱ ሼ ሌሲ በ89ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ለብራይተን አንድ ጎል ያስቆጠረው ብራጃን ግሩዳ የጨዋታ ኮከብ ሆኖ ተመርጧል። ውጤቱን ተከትሎ ብራይተን ወደ አራተኛ ዙር አልፏል። የ13 ጊዜ የኤፍኤ ካፕ አሸናፊ ማንችስተር ዩናይትድ በሶስተኛ ዙር ከውድድሩ ተሰናብቷል። ዛሬ በተደረገው ሌላኛው ጨዋታ አርሰናል ፖርትስማውዝን 4 ለ 1 አሸንፏል። በፍራተን ፓርክ በተካሄደው ጨዋታ ጋብርኤል ማርቲኔሊ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሲሰራ የፖርትስማውዙ አንድሬ ዶዜል በራሱ ላይ ቀሪዋን ግብ ለአርሰናል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ኮልቢ ቢሾፕ ለፖርትስማውዝ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አስቆጥሯል። 14 ጊዜ ዋንጫ በማንሳት የውድድሩ ስኬታማ ክለብ የሆነው አርሰናል ወደ አራተኛ ዙር አልፏል። ሶስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው የኤፍኤ ካፕ የሶስተኛ ዙር መርሃ ግብር እስከ ጥር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የወቅቱ የኤፍኤ ካፕ አሸናፊ ክሪስታል ፓላስ ትናንት በማክስፊልድ 2 ለ 1 ተሸንፎ ከውድድሩ ውጪ ሆኗል። 155 ዓመታትን ያስቆጠረው ኤፍኤ ካፕ የዓለም አንጋፋው የክለቦች ውድድር ነው።
በኤል ክላሲኮ ደርቢ ባርሴሎና ሪያል ማድሪድን በማሸነፍ የስፔን አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫን አነሳ
Jan 11, 2026 93
አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2018(ኢዜአ)፦ በስፔን የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ባርሴሎና ሪያል ማድሪድን 3 ለ 2 አሸንፏል። ማምሻውን በሳዑዲ አረቢያ ኪንግ አብዱላህ ስፖርትስ ሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ራፊኒያ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ሮበርት ሌዋንዶስኪ ቀሪዋን ጎል ለባርሴሎና ከመረብ አሳርፏል። ቪኒሺየስ ጁኒየር እና ጎንዛሎ ጋርሺያ ለሪያል ማድሪድ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በ91ኛው ደቂቃ የባርሴሎናው ፍራንኪ ዲ ዮንግ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። የባርሴሎናው ራፊኒያ በውድድር ዓመቱ በሁሉም ውድድሮች ያስቆጠራቸውን ግቦች ወደ 11 ከፍ አድርጓል። በጨዋታው ባርሴሎና በኳስ ቁጥጥር ብልጫ ቢወስድም ሁለቱም ቡድኖች በቁጥር ተቀራራቢ የግብ እድሎችን ፈጥረዋል። ጨዋታው አዝናኝ እና ሳቢ ፉክክር ተደርጎበታል። ውጤቱን ተከትሎ ባርሴሎና ለ16ኛ ጊዜ የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫን አንስቷል። የባለፈው ዓመት ክብሩንም ማስጠበቅ ችሏል። ባርሴሎና ለበርካታ ጊዜ ውድድሩን በማሸነፍ ስኬታማ ክለብ ነው። ሪያል ማድሪድ 13 ጊዜ ዋንጫውን በማንሳት ይከተላል። የስፔን የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ በስፔን ላሊጋ እና በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ በተመሳሳይ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃን የያዙ ክለቦች የሚሳተፉበት ውድድር ነው።
የስፖርት ቱሪዝም መጠናከር ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መነቃቃት ፋይዳው የጎላ ነው
Jan 11, 2026 89
ደብረብርሃን ፤ጥር 3/2018 (ኢዜአ) ፡- ስፖርት ጤናማና አምራች ዜጋን በመፍጠር የአካባቢውን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ምርታማነት ለማሳደግ የጎላ ፋይዳ አለው ሲሉ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በደሉ ውብሸት ገለጹ። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 2018 የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮች ዛሬ በደብረብርሃን ከተማ ተካሂደዋል። ውድድሮቹም የ6 ኪሎ ሜትር የሴቶችና ወንዶች ሩጫ እና የ22 ኪሎ ሜትር የዱላ ቅብብልን ያካተተ ነው። የደብረብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በእለቱ እንደገለጹት ስፖርት ጤናማና አምራች ዜጋን በመፍጠር ለአካባቢው ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ምርታማነት እድገት የጎላ ፋይዳ አለው። በተጨማሪም ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ ስፖርተኞችንና ተመልካቾችን በማገናኘት ለማህበራዊ ትስስር መጠናከር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በደብረ ብርሃን የተካሄደው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያም የከተማዋን እድገት፣ የመስህብ ስፍራዎችና ጸጋዎችን ለማስተዋወቅ መልካም እድል የሚፈጥር በመሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የቅርስ ጥበቃና ቱሪዝም ቡድን መሪ አቶ አክሊል ጌታቸው እንዳሉት ከተማዋ ያላት የአየር ንብረት ለስፖርታዊ ውድድሮች አመቺ ነው። ዛሬ የተካሄደው የስፖርት ውድድርም ወንድማማችነትን ለማጠናከርና ያሉ የተፈጥሮ ፀጋዎችን ለማስተዋወቅ የሚያግዝ በመሆኑ አዘጋጆቹን አመስግነዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የኮሙኒኬሽን ሀላፊ ወይዘሮ ሃና ገብረስላሴ በበኩላቸው ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ ህፃናትን፣ ወጣቶችንና ታዋቂ አትሌቶችን ያሳተፈ ውድድር መካሄዱን ገልጸዋልⵆ ውድድሩም የ6 ኪሎ ሜትር የሴቶችና ወንዶች ሩጫ እና የ22 ኪሎ ሜትር የዱላ ቅብብልን ያካተተ እንደነበር አንስተዋል። በ6 ኪሎ ሜትር የወንዶች ሩጫ ውድድር 1ኛ የወጣው ስጦታው ሰማኸኝ እንዳለው እንደዚህ ያለ ውድድር ያልታወቁ አትሌቶች የሚታዩበት በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በአብዛኛው የኢትዮጵያ አካባቢዎች ደረቅና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jan 12, 2026 22
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በአብዛኛው የኢትዮጵያ አካባቢዎች ደረቅና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ አንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፣በሚቀጥሉት አሰር ቀናት አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ክፍሎች ደረቅና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሀዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል። የበጋው ደረቅ ጸሃያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች እንደሚስተዋልና የለሊትና የማለዳው ቅዝቃዛ ከአምስት ዲግሪ ሼልሲየስ በታች እንደሚሆን አመልክቷል። ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑ የደቡብና የደቡብ ምስራቅ አካባቢዎችደረቅ ሆነው እንደሚቆዩም የትንበያ መረጃው ያመለክታል። በሌላ በኩል በደቡብ ምዕራብ፣የምዕራብና የመካከለኛው እንዲሁም ሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ አንጻራዊ የእርጥበት መጠንና የደመና ሽፋን ጥንካሬ ሊኖራቸው እንደሚችል በትንበያው ተመላክቷል።
በኦሮሚያ ክልል በ32 ሺህ የችግኝ ማፊያ ጣቢያዎች ችግኝ የማዘጋጀት ስራ እየተከናወነ ነው
Jan 12, 2026 77
አዳማ ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በ32 ሺህ የችግኝ ማፊያ ጣቢያዎች በክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የሚተከሉ ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ። በክልሉ ግብርና ቢሮ የደን ልማትና እንክብካቤ ዳይሬክተር አቶ ከተማ አብዲሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የተፈጥሮ ልማትና ሀብት ስራ ለምርታማነት እንዲሁም ለአካባቢ ጥበቃ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተጎዱና የተራቆቱ መሬቶች እንዲያገግሙ፣ የደረቁ ኃይቆች፣ ወንዞችና ጅረቶች እንዲመለሱ ማድረጉንም ገልጸዋል። በተያዘው በጋ ወራትም በ32 ሺህ የችግኝ ማፊያ ጣቢያዎች ለኢኮኖሚ፣ ለምግብነት ፣ለደን ሽፋንና ለውበት የሚውሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። ከችግኝ ማፊያ ጣቢያዎቹ ጎን ለጎን የክልሉ አርሶ አደሮችም በችግኝ ዝግጅቱ እየተሳተፉ መሆኑን ጠቁመዋል። በክልሉ ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር እየተዘጋጁ ካሉ ችግኞች ውስጥ ለፍራፍሬ፣ ለጥምር ደን አገልግሎት፣ ለአፈር ለምነትና ለውበት የሚውሉ 60 በመቶ ሲሸፍኑ ቀሪዎቹ 40 በመቶ ለደን ሽፋን አገልግሎት እንደሚውሉ ገልጸዋል። ባለፈው ክረምት ከተተከሉት ችግኞች ውስጥ በመጀመሪያው ዙር ቆጠራ ከ90 በመቶ በላይ መጽደቁንም ጠቁመዋል።
የተፈጥሮ ሀብትን በመጠበቅና በመንከባከብ የለማች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ይገባል
Jan 12, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የተፈጥሮ ሀብትን በመጠበቅ፣ በመንከባከብና በአግባቡ በመጠቀም የለማች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የአሁኑ ትውልድ ሃላፊነት መሆኑ ተገለጸ። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ዘንድሮ የሚካሄደውን የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራን አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። የቢሮው ሃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ እንደገለጹት፤ በክልሉ በዘንድሮው ዓመት 6 ሺህ 386 ተፋሰሶች ላይ 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር በሚሆነው መሬት ላይ የተፈጥሮ ሀብት ልማት፣ ጥብቃና እንክብካቤ ሥራ ይከናወናል። "የአካባቢ ልማት፣ እንክብካቤና ጥበቃ ለሀገር ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው የዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ከነገ ጥር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ60 ተከታታይ ቀናት የሚከናወን መሆኑንም አመልክተዋል። የተፈጥሮ ሀብትን በመጠበቅ፣ በመንከባከብና በአግባቡ በመጠቀም የለማች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የአሁኑ ትውልድ ሃላፊነት እንደሆነ የገለጹት አቶ ጌቱ፤ ለልማት ስራው ስኬታማነት አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራ እና የባለሙያ ስልጠና መከናወኑን ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት በክልሉ በተከናወኑት የተፋሰስ ልማትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኝ ተከላ ስራዎች ክልሉ የነበረው የደን ሽፋን ማደጉን ገልጸዋል። በዚህም ደርቀው የነበሩ ምንጮችና ኩሬዎች እንዲያገግሙ እና በበርካታ አካባቢዎች ላይ የአየር ንብረትና የመሬት ስነ ምህዳር እንዲሻሻል ማድረጉን ተናግረዋል። በዚህም ቀድሞ ለእርሻ አመቺ ያልነበሩ መሬቶች ጭምር ለግብርና ሥራ እየዋሉ በመምጣታቸው በክልሉ ወጣቶችና አርሶ አደሮች ተደራጅተው በልዩ ልዩ የግብርና ስራዎች ላይ በመሰማራት ምርትና ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ውጤት እየታየ መምጣቱን አመልክተዋል። በበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት በተከናወነባቸው ቦታዎች ላይ በክረምቱ ወራት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ገልጸው፤ ዘንድሮ በሚካሄደው የተፋሰስ ልማት ስራም የክልሉ ህዝብ በሙሉ አቅሙ በመሳተፍ ውጤታማ ስራ እንዲያከናውን አቶ ጌቱ ጥሪ አቅርበዋል። የዘንድሮው የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና እንክብካቤ ስራ በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በነገው እለት የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በቡኖ በደሌ ዞን ይጀመራል።
በድሬደዋ አስተዳደር የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ስራ ተጀመረ
Jan 11, 2026 140
ድሬደዋ፣ጥር 3/2018(ኢዜአ) ፡-በድሬደዋ አስተዳደር 38ቱ የገጠር ቀበሌዎች የበጋ ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ዛሬ መካሄድ ጀመረ። በአስተዳደሩ አራቱ የገጠር ክላስተሮች ዛሬ በተጀመረውና ለአንድ ወር በሚዘልቀው የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ሥራ 5ሺህ 550 ሄክታር የሚሸፍን የተፋሰስ ልማት እንደሚከናወን ታውቋል። በአሰሊሶ ገጠር ክላስተር ገንደ ሪጌ ቀበሌ ተገኝተው የተፋሰስ ልማቱን ያስጀመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እና የአስተዳደሩ ምክርቤት ምክትል አፈጉባኤ ወይዘሮ ከሪማ አሊ ናቸው። የድሬደዋ አስተዳደር ምክርቤት አፈጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር፣ የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬደዋ አስተዳደር ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተቀሩት ክላስተሮች ተገኝተው የተፋሰስ ልማቱን አስጀምረዋል። "የተቀናጀ የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት፤ ለግብርና ሽግግር ስኬት" በሚል መሪ ሃሳብ በተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ላይ የተለያዩ የአፈርና የውሃ ሃብትን በዘላቂነት መጠበቅና ማበልፀግ የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚካሄዱም በወቅቱ ተገልጿል። ለአንድ ወር በሚካሄደው የተፋሰስ ልማት ስራው ከ37ሺህ 900 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉም ታውቋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ውኃ ለአፍሪካ የኅልውና ጉዳይ ነው - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Jan 12, 2026 84
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ ውኃ ሁሉንም ዘርፍ የሚነካ አህጉራዊ የኅልውና ጉዳይ መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የሕብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ስብሰባው"ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሐሳብ የሚደረግ ነው። በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ፣ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት ትኩረቱን ያደረገው በውኃ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ውኃ በሁሉም አይነት እጅጉን ወሳኝ የሆነ ሀብት እና የኅልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ አህጉራዊ ግቦቹን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አስገንዝበዋል። በብራዚል ቤለም የተካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) ትኩረት ከተሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል አንዱ መሆኑንም አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በምታዘጋጀው 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ውኃ አንዱ አጀንዳ እንደሚሆንም ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማዘጋጀት በመመረጧ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ያሉ ሲሆን፤ ለጉባኤው ስኬታማነት ሕብረቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ሰላም እና ደኅንነት የአፍሪካ አንገብጋቢ አጀንዳ መሆኑን የገለጹት ሊቀ መንበሩ ሱዳን፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሊቢያን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ኢ-ሕገመንግሥታዊ ለውጦች አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው፤ ሀገራት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንዲያከብሩ አሳስበዋል። የአፍሪካ ሕብረት ተቋማዊ ሪፎርም እና ኢኮኖሚያዊ ትሥሥርን ጨምሮ ለአህጉራዊ አጀንዳዎች እየሠራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። አህጉራችን ፈተናዎች ቢኖሩባትም በጋራ ከቆምን እናልፋቸዋለን ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የዛሬው ስብስባ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን፤ የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ መሆኑ ይታወቃል።
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ይጀመራል
Jan 12, 2026 145
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚደረግ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣የሕብረቱ አባል አገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብስባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል አገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
የቻይና አፍሪካ ትብብር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል
Jan 8, 2026 142
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማሕሙድ አሊ ዩሱፍ ከቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ጋር ውይይት አካሄዱ። ውይይቱ እያደገ የመጣው የቻይና አፍሪካ ትብብርን ማጠናከር ላይ ያለመ ነው ተብሏል። ቻይና የአፍሪካ እውነተኛ አጋር መሆኗን የገለፁት የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ያተኮረው ፖሊሲ ጠንካራ ወዳጅነት እንዲፈጠር ማድረጉን ገልፀዋል። የቻይና አፍሪካ ግንኙነት በተለያዩ የትብብር ማዕቀፎች እያደገ መምጣቱንም ተናግረዋል። ከውይይቱ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ሁለቱ ወገኖች የዓለም ደቡባዊ ቀጣና (Global South) ሀገራትን መብትና ጥቅም ለማስከበር፣ የሉዓላዊነትን ክብር ለመጠበቅ እና ዓለም አቀፍ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በጋራ ለመሥራት መስማታቸውን አስታውቀዋል። በውይይቱ ወቅት የቻይናን የአምስት ዓመት የልማት ዕቅድ ከአፍሪካ ኅብረት የ2063 አጀንዳ ሁለተኛው የዐሥር ዓመት ትግበራ ጋር በማጣጣም ዘመናዊነትን ለማምጣት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ምክክር መደረጉ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነቶችን ጨምሮ፣ ቻይና ያቀረበቻቸውን ዓለም አቀፍ የደኅንነትና የልማት ተነሳሽነቶች በጋራ ለመደገፍ ከስምምነት መድረሳቸውን ኢቢሲ ዘግቧል። በተጨማሪም የተፈረሙ የትብብር ስምምነቶችን በተግባር በመተርጎም እና የንግድ ልውውጥን በማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት በጋራ መግለጫቸው አረጋግጠዋል።
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ በቀጣዩ ሳምንት ይጀመራል
Jan 8, 2026 144
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ(PRC) መደበኛ ስብሰባው ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ያተኮረ ነው። በስብሰባው የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብሰባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብሰባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 488
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 451
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 670
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 825
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 453
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 410
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 1068
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3405
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3019
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1918
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7735
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6215
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
አማድ ዲያሎ - የአፍሪካ እግር ኳስ ብሩህ ተስፋ
Jan 9, 2026 227
ተጫዋቹ አዲሱ ሳሙኤል ኤቶ የሚል ስያሜ እየተሰጠው ይገኛል። ፍጥነቱን ከዲዲየር ድሮግባ ጋር ያነጻጽሩታል። ለተጋጣሚ ተጫዋቾች የራስ ምታት እና ፈተና የሆነውን ግራ እግሩን ከሌላኛው የግራ እግር ምትሃተኛ ሪያድ ማህሬዝ ጋር የሚያወዳድሩም አልጠፉም። በዚህ አካሄዱ ከቀጠለ ያለ ምንም ጥርጥር ወደፊት በእግር ኳስ ከምንመለከታቸው ኮከቦች አንዱ ሊሆን ይችላል እየተባለለት ይገኛል። ይህ ተጫዋች በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ዓመታት ታሪክ ሀትሪክ የሰራ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ተጫዋች ነው። እያወራን የምንገኘው የማንችስተር ዩናይትድ 16 ቁጥር ማልያ ለባሽ አማድ ዲያሎ ነው። የ23 ዓመቱ ኮትዲቯራዊ ተስፈኛ ተጫዋች በቀያዮቹ ሴጣኖች እያሳየ ያለው ብቃት ከብዙዎች ዘንድ ሙገሳ አስችሮታል፣ አድናቆት እንዲጎርፍለት አድርጓል። ወደ ኋላ መለስ እንበልና የአማድ ዲያሎን መነሻ እንመልከት። ካሜሮን ከአዘጋጇ ሞሮኮ ለግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው አማድ የተወለደው እ.አ.አ ጁላይ 11 2002 በኮትዲቭዋር መዲና አቢጃን ነው። ተጫዋቹ በአፍሪካ ምድር ቢወለድም ገና በህጻንነት እድሜው ነበር ወደ ጣልያን የተሰደደው። የእግር ኳስ ህይወቱን የጀመረው እ.አ.አ በ2014 በጣልያን ሬጂዮ ኢሚሊያ ግዛት በሚገኘው ቦካ ባርኮ የታዳጊ ቡድን ነው። ቡድኑን በተቀላቀለበት ዓመት የገና በዓል (ክሪስማስን) በማስመልከት በተካሄደ ውድድር ላይ በ12 ዓመቱ ኮከብ ግብ አግቢ ሲሆን ያሳየው አስደማሚ ብቃት የብዙዎችን ቀልብ ሳበ። ይህ የገና በዓል ውድድር አማድን እ.አ.አ በ2015 በቦካ ባርኮ ቡድን እንዲመዘገብ አደረገው። ተጫዋቹ በቡድኑ ብዙም አልቆየም። የበርካታ የጣልያን ሴሪአ ክለቦች አይን አረፈበት። ብዙም ሳይቆይ በዛው በ2015 ወደ ጣልያኑ አትላንታ አመራ። አማድ ከእ.አ.አ 2015 እስከ 2019 ለአትላንታ ታዳጊ ቡድን የተጫወተ ሲሆን እ.አ.አ 2019 እና 20 ለዋናው ቡድን ተጫውቷል። ለዋናው ቡድን አራት ጨዋታዎችን አድርጎ ማስቆጠር የቻለው አንድ ግብ ብቻ ነው። የእንግሊዙ ክለብ ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹ በጣልያኑ ክለብ ባሳየው ብቃት በ18 ዓመት እድሜው እ.አ.አ ጃንዋሪ ወር 2021 በአምስት ዓመት ኮንትራት በ37 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዩሮ አስፈርሞታል። ተጫዋቹ ወደ ማንችተር ሲመጣ ቀጥታ ወደ ዋናው ቡድኑ አልተቀላቀለም። በቡድኑ ከ23 ዓመት በታች ጨዋታውን ማድረግ ጀመረ። አማድ የመጀመሪያ ጨዋታውን ለማንችስተር ያደረገው እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 18 2021 ቡድኑ ከሪያል ሶሲዬዳድ ጋር ባደረገው የዩሮፓ ሊግ ጨዋታ ነው። በዛው ዓመት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እና አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ላይ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ዲያሎ ከእ.አ.አ 2022-2023 ባለው ጊዜ ሬንጀርስ እና ሰንደርላንድ በውሰት የተጫወተ ሲሆን በቡድኖቹ ባደረጋቸው 47 ጨዋታዎች 16 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023/24 አማድ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ በመመለስ በድጋሚ መጫወት ጀምሯል። በክለቡም ድንቅ ብቃቱን እያሳየ መምጣት ጀመረ። እ.አ.አ ጥር 17 2025 ማንችስተር ዩናይትድ ከሊጉ ከወረደው ሳውዝሃምፐን ጋር በነበረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር በ12 ደቂቃ ውስጥ ሶስት ግቦችን አስቆጥሮ ሀትሪክ በመስራት ቡድኑ 3 ለ 1 አንዲያሸንፍ ያደረገበት መንገድ አድናቆት አስችሮታል። በዚህም አማድ በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ታሪክ የመጀመሪያ ሀትሪክ የሰራ አፍሪካ ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። አማድ በቀያዮቹ ሴጣኖች ማልያ እስከ አሁን ባደረጋቸው 53 ጨዋታዎች 11 ግቦችን አስቆጥሯል። ተጫዋቹ ከክለቡ በተጨማሪ ለኮትዲቯር ብሄራዊ ቡድን በመጫወት ላይ ይገኛል። እ.አ.አ 2021 ኮትዲቯር ከኒጀር ጋር ባደረገችው ጨዋታ በ86ኛው ደቂቃ ተቀይሮ በመግባት ለብሄራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ለሀገሩ እስከ አሁን ባደረጋቸው 15 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። የመጀመሪያ ጎሉን ኮትዲቯር በ2021 በወዳጅነት ጨዋታ ቡርኪናፋሶን 2 ለ 1 ስታሸነፍ ነበር ያስቆጠረው። አማድ ዲያሎ ዘንድሮ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ድንቅ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል። አማድ በውድድሩ ላይ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች ሶስት ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን አንድ ለግብ የሚሆን ግብ አመቻችቶ አቀብሏል። ኮትዲቯር ከሞዛምቢክ፣ ካሜሮን እና ቡርኪናፋሶ ጋር ባደረገቻቸው ጨዋታዎች የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተምርጧል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቯር ሩብ ፍጻሜ እንድትደርስ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። ኮትዲቯር ከግብጽ በሩብ ፍጻሜው ነገ ከግብጽ ጋር ምሽት አራት ሰዓት ላይ በአጋዲር ስታዲየም የምታደርገው ጨዋታ በጉጉጉት ይጠበቃል። ሀገሩ በጠዋታው ላይ ከአማድ ብዙ ትጠብቃለች። ወደ ክለብ እንቅስቃሴው ስንመለስ አማድ በማንችስተር ዩናይትድ ስብስብ ውስጥ ቁልፍ የሚባል ተጫዋች ነው። ፈጣን ኳስን የማንከበላል ክህሎቱ፣ ፍጥነቱ ፣ የቴክኒክ አቅሙ፣ ጨዋታን የማንበብ ብቃቱ እና ሁለቱንም እግሩን የመጠቀም አቅሙ አልፎም ተጫዋቾችን በቄንጥ የሚያልፍበት መንገድ ተጫዋቹን እያስወደሰው ነው። አማድ ዲያሎ ከክንፍ ተጫዋችነቱ ባሻገር የአጥቂ አማካይ ሆኖ መጫወትም ይችላል። እ.አ.አ በ2020 የ18 ዓመት ልደቱን ተከትሎ ተጫዋቹ ስሙን ከአማድ ትራኦሬ ወደ አማድ ዲያሎ አስቀይሯል። አማድ ካለው ድንቅ ብቃት አንጻር ወደፊት በክለብ እና ብሄራዊ ቡድን ደረጃ ድንቅ ጊዜን ካሳለፉ ታዋቂ የአፍሪካ ተጫዋቾች ተርታ የመሰለፉ ጉዳይ አያጠራጥርም።
በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ብዙ ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን ያቀበሉ ተጫዋቾች
Jan 5, 2026 244
በእግር ኳስ ጨዋታ ከግብ አስቆጣሪዎች ጀርባ ኳስን ፍትፍት አርገው ጨርሰው የሚያቀብሉ ተጫዋቾች አሉ። አንድ ተጫዋች ግብ ሲያገባ ከማግባቱ ባልተናነሰ ማን ኳሱን አቀበለው? የሚለው ጥያቄ በተመልካቾች ይነሳል። በእግር ኳስ እድገት ውስጥ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለጎል ኳስ አመቻችተው የሚያቀብሉ ተጫዋቾች ትልቅ ዋጋ ይሰጣቸዋል። ማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪምን አሰናበተ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች እየተካሄዱ ይገኛሉ። የ33 ዓመቱ የሴኔጋል አምበል ሳዲዮ ማኔ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ካስቆጠረው አንድ ግብ በተጨማሪ ሶስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል የቀዳሚነቱን ስፍራ ይዟል። ማኔ ሴኔጋል ለሩብ ፍጻሜ እንድታልፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ ትልቅ የሚባል ነው። ስምንት ተጫዋቾች በተመሳሳይ ሁለት ለግብ የሚሆኑ ግቦችን አመቻችተው አቀብለዋል። ናይጄሪያውያኑ አዴሞላ ሉክማን እና አሌክስ ኢዎቢ፣ የሞሮኮው አዝዲን ኡናሂ፣ የአልጄሪያው አኒስ ሃጂ-ሙሳ፣ የቡርኪናፋሶው ዳንጎ ኡታራ፣ የቱኒዚያው ሃኒባል ሜጅብሪ፣ የደቡብ አፍሪካው ላይል ፎስተር እና የታንዛንያ ኖቫቱስ ሞሮሺ በሁለት ግቦች ላይ እጃቸው ያለበት ተጫዋቾች ናቸው። የናይጄሪያው የክንፍ የመስመር ተጫዋች አዴሞላ ሉክማን ሁለት ግቦችን በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አስቆጥሯል። የኮትዲቯሩ ክርስቶፈር ኦፔሪ እና የናይጄሪያው ሳሙኤል ቹኩዌዜ በተመሳሳይ አንድ አንድ ግቦች ከመረብ ላይ እንዲቆጠሩ የቀጥታ ተሳትፎ አድርገዋል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬን (ካፍ) የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ኮከብ ተጫዋች ምርጫ ላይ ካስቀመጣቸው መመዘኛ መስፈርቶች አንዱ ማን ብዙ ለጎል የሚሆን አቀበለ? የሚለው ይገኝበታል። 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እስከ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የግብ አግቢዎችና የኳስ አቀባዮቹ ፉክክር በያዘው ግለት ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል።