አርእስተ ዜና
ከኦቲዝም ጋር የሚኖሩ ዜጎችን የትምህርት እድል ተጠቃሚ ለማድረግ የጋራ ርብርብ ይጠይቃል
Mar 28, 2023 29
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ) ከኦቲዝም ጋር የሚኖሩ ዜጎችን የትምህርት እድል ተጠቃሚ በማድረግ ይበልጥ አምራች ዜጋ እንዲሆኑ ሁሉም አካላት በትብብር እንዲሰሩ በጉዳዩ ላይ የሚሰሩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጠየቁ። ኒያ ፋውንዴሽን፣ ነህሚያ ኦቲዝም ማዕከል፣ ብራይት ኦቲዝም ማዕከል ሃዋሳ፣ ቤቴል አዳማ ኦቲዝም ማዕከልና ምሉዕ ፋውንዴሽን በጋራ በመሆን በኢትዮጵያ በኦቲዝም የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በአሳሳቢ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል። በኒያ ፋውንዴሽን የጆይ ኦቲዝም ማዕከል ዋና ሥራ አስኪያጅ እሌኒ ዳምጠው በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ የኦቲዝም እክል ብዙም ትኩረት ባለመሰጠቱ በቤተሰቦቻቸውና በማኅበረሰቡ ብዙ እንግልት እየደረሰባቸው ይገኛሉ። በተለይ ደግሞ የአገሪቱ የትምህርት ሥርዓት ከኦቲዝም ጋር ለሚኖሩ ዜጎች በቂ የሆነ እድል የሚሰጥ አይደለም ብለዋል። በዚህም ምክንያት ከራሳቸው አልፈው ለአገርና ቤተሰብ አለኝታ መሆን የሚችሉ በርካታ ዜጎች ባክነው ይቀራሉ ነው ያሉት። ይህን ችግር መነሻ በማድረግ ጆይ ኦቲዝም ማዕከል አስራ ሁለት ልጆችን አስተምሮ በማብቃት በግቢው ውስጥ ሥራ እንዲይዙ አደርጓል ብለዋል። በዚህም እነዚህ ዜጎች የራሳቸውን ህይወት ከመደጎም ባለፈ ከደሞዛቸው ተቆራጭ እየሆነ ለመንግሥት ግብር ማስገባት መጀመራቸውን ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅትም 80 ልጆችን በማቀፍ የማስተማርና የመንከባከብ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አመላክተዋል።   በመሆኑም የኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ከኦቲዝም ጋር የሚኖሩ ዜጎችን ታሳቢ ያደረገ መሆን እንደሚገባው ነው ያመላከቱት። የነህሚያ ኦቲዝም ማዕከል ዋና ሥራ አስኪያጅ ራሔል አባይነህ በበኩላቸው እነዚህ ልጆች ድጋፍና ትምህርት ከተሰጣቸው እንደማንኛውም ሰው አምራች ዜጋ መሆን እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ዜጎቹ በተለይም በትምህርት ሥርዓት ውስጥ የሚካተቱበትን ሁኔታ ለማጠናከር መስራት ይገባል ብለዋል። ብራይት ኦቲዝም ማዕከል ሃዋሳ ዋና ሥራ አስኪያጅ ትዕግስት አበበ በበኩላቸው ተቋማቸው እነዚህ ዜጎች ከኢኮኖሚ ጥገኝነት እንዲወጡ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የትምህርት እድል እንዲሰጣቸው በማድረግ ራሳቸውን እንዲችሉ ሁሉም ሊተባበር ይገባዋል ነው ያሉት። የቤቴል አዳማ ኦቲዝም ማዕከል ሥራ አስኪያጅ ገነት ንጉሴና የምሉዕ ፋውንዴሽን ኦቲዝም ማዕከል ዋና ሥራ አስኪያጅ ትዕግስት ሃይሉ በበኩላቸው፤ ማዕከላቸው በኦቲዝም የተያዙ ልጆችን በማሰባሰብ የህይወት ክህሎት ሥልጠና እየሰጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። እነዚህ ዜጎች ራሳቸውን ብቁ ለማድረግ የሚያስችላቸውን ድጋፎች እንዲያገኙ መሥራት የሁሉም ሃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል። አምስቱ የኦቲዝም ማዕከላት የኦቲዝምን ችግር ያለባቸውን ዜጎች መብት ለማስከበርና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲን ለመመሥረት መግባባት ላይ ደርሰዋል። በቀጣይም ሌሎች በመስኩ የተሰማሩ ተቋማትን እያካተቱ እንደሚሔዱ ተናግረዋል።  
የሕዝቦችን ሁለንተናዊ ትስስር ለማጠናከር እንሰራለን - የኦሮሚያና የሶማሌ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳደሮች  
Mar 28, 2023 35
ጅግጅጋ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ) ጅግጅጋ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ) ፡- በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች ሕዝቦች መካከል የቆየውን ሁለንተናዊ ትስስር በልማት ለማጠናከር እንደሚሰሩ የክልሎች ርዕሳነ መስተዳደሮች ገለጹ። ርዕሳነ መስተዳደሮቹ ይህንን የገለጹት፤ የኦሮሚያ ክልል በመደበው 40 ሚሊዮን ብር ውጪ በጅግጅጋ ከተማ የተገነባ "ካህ" ተብሎ የተሰየመውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዛሬ በጋራ ሲመርቁ ነው።   የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ በጅግጅጋ ከተማ የተገነባው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሁለቱን ክልሎች ህዝቦች በልማት ለማስተሳሰር ከተከናወኑ ስራዎች አንዱ ማሳያ ነው። አቶ ሽመልስ "የሁለቱን ሕዝቦች የቆየ ትስስር ለማጠናከርና በልማት ለማስተሳሰር ያስገነባነው ይህ ትምህርት ቤት በቀጣይ አገርን የሚመሩ ወጣት ምሁራን የሚወጡበት ይሆናል" ብለዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድ በበኩላቸው፤ "የኦሮሚያ ክልል ያስገነባው ትምህርት ቤት ከወንድም ሕዝብ የተደረገልን ትልቅ ስጦታ ነው" ብለዋል። "የሁለቱ ሕዝቦች ያላቸው ሁለንተናዊ ትስስር በልማት ለመደገፍና በጋራ ለማደግ የያዙትን ጥረት ስኬታማ መሆኑን ይህ ትምህርት ቤት በማሳያነት የሚጠቀስ ነው" ሲሉም ገልጸዋል። ትምህርት ቤቱ የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች እንዲማሩበት ይሰራል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ትምህርት ቤቱን ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ጋር ለማስተሳሰር መታቀዱንም ጠቁመዋል። ባለ ሁለት ወለል ሕንጻ የሆነው ትምህርት ቤት የመማሪያ ክፍል፣ ቤተ-መጻሕፍት ፣ ቤተ-ሙከራና የአስተዳደር ክፍሎችን ያካተተ ነው። በስነ ስርዓቱ ላይ የሁለቱ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ፣ የጎሳ መሪዎች፣ የኃይማኖት አባቶች ፣ወላጆችና ተማሪዎች፣ ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያና ጃፓን በሆርቲካልቸር ልማት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ
Mar 28, 2023 27
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያና ጃፓን በሆርቲካልቸር ልማት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ የአነስተኛ አርሶ አደሮችን የሆርቲካልቸር አቅም ማጎልበቻ ፕሮጀክት ሁለተኛ ምዕራፍ ተፈጻሚ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል። የግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር መለሰ መኮንንና የጃፓን አለም አቀፍ የልማት ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የኢትዮጵያ ተወካይ ሞሪሃራ ካሱኪ ስምምነቱን ተፈራርመዋል። አነስተኛ አርሶ አደሮች የሆርቲካልቸር አቅም ማጎልበቻ ፕሮጀክት በምዕራፍ አንድ አማራ እና ኦሮሚያ ክልል ሲተገበር መቆየቱ ተገልጿል። በስምምነቱ መሰረት የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ምዕራፍ በደቡብና ሲዳማ ክልሎች እንደሚተገበር ተጠቁሟል። ሚኒስትር ዲኤታው ዶክተር መለሰ መኮንን የጃፓን መንግስት ሆርቲካልቸር ልማት ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ለመስራት ያለውን ፍላጎት አድንቀዋል፡፡ የጃፓን አለም አቀፍ የልማት ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የኢትዮጵያ ተወካይ ሞሪሃራ ካሱኪ በፕሮጀክቱ በምዕራፍ አንድ የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። በምዕራፍ ሁለት የፕሮጀክቱ ትግበራ ጃይካ ለአነስተኛ አርሶ ደሮች በሆርቲካልቸር ልማት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለጻቸውን ከግብርና ሚኒስቴር ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀገራዊ የለውጥ ሂደቱን ማጠናከር እንደሚገባ ምሁራን አመለከቱ
Mar 28, 2023 29
ድሬደዋ መጋቢት 19 /2015(ኢዜአ) ፡- በየደረጃው ለሚያጋጥሙ ችግሮች የተቀናጀ መፍትሔ በመስጠት የተጀመረውን ሀገራዊ የለውጥ ሂደት ማጠናከር እንደሚገባ ምሁራን አመለከቱ። ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲና የተለያዩ ኮሌጆች የተወጣጡ ምሁራን በሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ከድሬዳዋ አስተዳደር አመራሮች ጋር ተወያይተዋል። ምህራኑ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት ፤ መንግስት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከህብረተሰቡ ጋር መወያየቱ ለሚያጋጥሙ ችግሮች የጋራ መፍትሄ ለማምጣት ያግዛል ። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የውጭና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደቻሳ ጋንፉሬ በሰጡት አስተያየት ፤ ባለፉት አራት ዓመታት የመጣው ሀገራዊ ለውጥና ተከትሎም የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሚስተዋሉ የኑሮ ውድነትና የማህበራዊ አገልግሎት ችግሮች ዜጎችን እያማረሩ በመሆናቸው የተቀናጀ መፍትሔ በመስጠት የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። ይህን መሠል ወቅታዊ ውይይት ማስቀጠል ዜጎች የሚሰማቸውን ከማሳወቅ ባሻገር ሁሉም የመፍትሔ አካል እንዲሆን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቁመዋል። መምህር ያሬድ ጥበቡ በበኩላቸው ፤ በለውጡ የተገኙ ሁሉን አቀፍ አበረታች ለውጦችና ውጤቶች ማጠናከር ላይ መረባረብ ይገባል ብለዋል። ለሚያጋጥሙ ችግሮች በተቀናጀ አግባብ መፍትሄ በመስጠት የለውጡን ሂደት ማስቀጠል እንደሚገባ አመልክተዋል። በተለይ በድሬደዋ የሚስተዋለው የኑሮ ውድነትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት መንግስት በአፋጣኝ የመፍትሄ እርምጃ መውሰድ እንዳለበትም ጠቁመዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር በነዳጅ ማደያዎች ውስጥ እየተስፋፋ ለሚገኘው ህገ ወጥና የተበላሸ አሰራር አፋጣኝ መፍትሔ በመስጠት ከትራንስፖርት አገልግሎት ጋር ለተያያዙ ችግሮች መፍትሄ መስጠት እንዳለበት የተናገሩት አቶ ወሰን ቢራቱ ናቸው። የአከባቢው ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል እንዲሁም ለሚስተዋለው የመልካም አስተዳደር ችግሮች የመፍትሔ አካል በመሆን የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል ። ውይይቱን ከመሩት መካከል የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፤ በድሬዳዋ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስና የለወጥ ሂደቱን ለማፅናት ጥናትን መሠረት ያደረገ የተቀናጀ ሁሉንአቀፍ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህን ተግባራት ከዳር ለማድረስ መሰል ውይይቶች በማስፋት ምሁራን ጨምሮ የሌሎችንም የህብረተሰብ ክፍሎችን ድጋፍና ተሳትፎ እንዲጠናከር ይሰራል ብለዋል። በተመሣሣይ በአስተዳደሩ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች ፣ዑጋዞችና አባገዳዎች እንዲሁም የንግዱ ማህበረሰብና ባለሃብቶች የተሳተፉበት ውይይቶች በሌሎች መድረኮች ተካሂደዋል ።  
ሙስናን ለመከላከል በተቋማት መካከል ትብብርና ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር ይሰራል - የፌደራል ሥነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን 
Mar 28, 2023 28
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ) ሙስናን ለመከላከል በተቋማት መካከል ትብብርና ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ የፌደራል ሥነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ገለጸ። ኮሚሽኑ ከ97 የፌደራል ተቋማት ለተውጣጡ ከ270 በላይ የሥራ ኃላፊዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና በቢሸፍቱ እየሰጠ ነው። ሥልጠናው የሙስና ወንጀል፣ ኦዲትና ሙስናን መከላከል፣ በሥነ-ምግባር ስትራቴጂ ዙሪያዎች ላይ ትኩረት አድርጓል ተብሏል።   የፌደራል ሥነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወዶ አጦ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ሙስናን ለመከላከል የተቀናጀ አሰራር መዘርጋትና ማጠናከር ወሳኝ ነው። በተናጠል የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ውጤት አለማምጣታቸውን ገልጸው ይህንን ክፍተት ለመሙላት የተቀናጀ አሰራር መጠናከር አለበት ብለዋል። በመሆኑም በተቋማት መካከል ያለው ቅንጅታዊ አሰራር ከተጠናከረ በአገር አቀፍ ደረጃ ሙስናን ለመከላከል የተጀመረው ጥረት ፍሬያማ እንደሚሆን ገልጸዋል። በአገሪቱ ማኅበራዊ ቀውስን በማስፋፋት ጉልህ ድርሻ የሚጫወተውን ሙስናን ሥነ-ምግባር ችግሮች ሊቀንሱ የሚችሉት በኅብረተሰቡ ተሳትፎ ጭምር መሆኑንም አስገንዝበዋል። ለሦስት ቀናት በሚቆየው በዚሁ ሥልጠና ከተቋማቱ የተውጣጡ የፀረ ሙስናና ሥነ-ምግባር ዳይሬክተሮች፣ የኦዲት ኃላፊዎች፣ የለውጥ አመራሮችና የሕግ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።    
የሚታይ
የዋጋ ንረትን ለመቀነስ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ነው--ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ
Mar 28, 2023 86
  አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ የዋጋ ንረትን ለመቀነስ በመንግስት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተለያዩ ጉዳዮች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ። ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል አንዱ የዋጋ ግሽበት ጉዳይን የተመለከተ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በምላሽ እና ማብራሪያቸው የዋጋ ግሽበቱን ለመቀነስ በመንግስት እየተተገበሩ የሚገኙ ስራዎችን ዘርዝረዋል። በዚህም ኢትዮጵያ ውስጥ ያጋጠመው የዋጋ ንረት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች እየጎዳ መሆኑን መንግስት በጽኑ ይገነዘባል ብለዋል። አሁን ላይ የታየው የዋጋ ንረት ችግር ላለፉት 20 ዓመታት የማያቋርጥ የዋጋ ንረት መፈጠሩ አንዱ ምክንያት መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሸማች እና አምራች መካከል ያለውን ክፍተት ማስተካከል ካለመቻሉም በላይ ጦርነት፣ ድርቅ፣ የአጋር አካላት እርዳታ መቀነስ እና ወደ ከተማ ፍልሰት መጨመር ለዋጋ ንረቱ መፈጠር ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸው ሲሉም አክለዋል። የዋጋ ንረቱን ለመቀነስ እየተተገበሩ የሚገኙ መፍትሄዎች የምርት አቅርቦት ላይ በስፋት መስራት፣ የምገባ ማእከል እና የማዕድ ማጋራት ስርዓትን ማስፋት ላይ እየተሰራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ የዋጋ ንረቱን መቀነስ የሚያስችል የተለያዩ ደጎማዎች እየተደረጉ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሳያነትም በነዳጅ ላይ ባለፉት 8 ወራት ከ50 ቢሊዮን ብር በላይ መደጎሙን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም 133 ሺህ ገደማ የሚሆኑ ተሸከርካሪዎች የድጎማው ተጠቃሚ ሆነዋል ነው ሲሉም አክለዋል።
ድንበር አካባቢ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሠላማዊ መንገድ በንግግር መፍታት ኢትዮጵያ ቅድሚያ የምትሰጠው ጉዳይ ነው--ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ
Mar 28, 2023 64
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ ድንበር አካባቢ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሠላማዊ መንገድ በንግግር መፍታት ኢትዮጵያ ቅድሚያ የምትሰጠው ጉዳይ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተለያዩ ጉዳዮች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ። ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል አንዱ ኢትዮጵያ ከሱዳንና ደቡብ ሱዳን ከምትዋሰንበት ድንበሮች ጋር በተያያዘ ያጋጠሙ ችግሮችን የተመለከተ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ ድንበር አካባቢዎች ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ለውይይትና ሠላማዊ መንገድ ቅድሚያ መሰጠቱን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር በሚያዋስናት ድንበር ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት ኮሚሽን ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። ከሱዳን ጋር ያለው ችግር በዘላቂነት የሚፈታው ድንበር የማካለሉ ጉዳይ እልባት ሲያገኝ መሆኑን ገልጸው እስከዛው ግለሰቦችና አርሶ አደሮች እንዳይጉላሉ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ጎን ለጎንም "የደቡብ ሱዳን መንግሥት ኢትዮጵያን ወሯል በሚል የሚነሳው አገላለጽ ትክክል አይደለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የደቡብ ሱዳን አርሶና አርብቶ አደሮች ድርቅ ገጥሞናል በሚል 20ሺህ ያህል ከብቶችን ነድተው ወደ ኢትዮጵያ ድንበር አልፈው መግባታቸውን አንስተዋል። ይህንንም በተመለከተ "ከአርሶና አርብቶ አደሩ ጋር ንግግር ተደርጓል፤ የሚያሰጋ ነገር አይፈጠርም" ሲሉም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ያረጋገጡት። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ ከደቡብ ሱዳን ድንበር ጋር በተያያዘ ያጋጠመውን ችግር በሁለቱ አገራት መካከል ውይይት በማድረግ ችግሩን ለመፍታት ከመግባባት ላይ ተደርሷል።
መንግስት ከየትኛውም ኃይል ጋር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ ነው-- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
Mar 28, 2023 49
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦መንግስት ከየትኛውም ኃይል ጋር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት በ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የስድስት ወራት ሪፖርት አስመልክቶ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ኦነግ ሸኔን በሚመለከት ባለፉት ጊዜያት ከአስር ጊዜ በላይ ንግግሮች መደረጉን ገልጸዋል። “የሰላም ጥሪውን በሚመለከት የኦሮሚያ ክልል የተጀመረ ሳይሆን እንደ ፓርቲ ተነጋግረን ነው የወሰነው፤የሰላም ጥሪው የዚሁ ንግግር ተቀጥያ ነው።” ብለዋል። ነገር ግን ቡድኑ አንድ የተሰባሰበ ኃይል አለመሆኑ ችግር መፍጠሩን አመልክተዋል። መንግስት ያለውን ችግር በሰላማዊ መንገድ እና በውይይት ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሁንና ይበልጥ የሰው ነፍስ እንዳይጠፋ ለመከላከል የጸጥታ ኃይሉ ጠንካራ ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። “መንግስት ከየትኛውም ኃይል ጋር ችግሮችን መፍታት የሚፈልገው በውይይትና በንግግር ብቻ ነው” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ወደ ተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
Mar 28, 2023 63
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ወደ ተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እየሰጡ ነው። ዛሬ እየተካሔደ በሚገኘው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛው መደበኛ ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት አሁን ላይ ሰላምን በተመለከተ ከዛሬ ስድስት ወር የተሻለ ሁኔታ አለ ብለዋል።   ወደተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገር ግን አንድ ርምጃ ወደፊት የወሰደ ሥራ ተሠርቷል ሲሉም ገልጸዋል። ባለፉት 50 እና 60 ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው ፖለቲካ የመተላለፍ፣ የሴራ እና የጉልበት ፖለቲካ እንደነበረ ገልጸው “ሰላም አስፈላጊ ነው ብለን በጽኑ እናምናለን፣ ሰላም እንደጦርነት ጀግንነት ይፈልጋል፣ ከጦርነት ያልተናነሰ ሥራ ድካም ይጠይቃል” ብለዋል። የረጋ ሰላማዊ ነገር እንዲሁ አይመጣም አዎንታዊ ሰላም በሀይል አይመጣም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምንጊዜም ሰላም ሲባል የአንድ ሰው ህይወት ማትረፍም ስለሆነ በዚህ ላይ መሥራት ይገባናል ብለዋል።
የሚዲያ ነፃነትን ያላግባብ በመጠቀም ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኃን ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Mar 28, 2023 66
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ የሚዲያ ነፃነትን ያላግባብ በመጠቀም ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኃን ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ፡፡ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የምክር ቤት አባላት በተለይም በአገሪቷ የተለያዩ አካባቢዎች የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ላይ ትኩረት በማድረግ ጥያቄዎችን አንስተዋል። በትግራይ ክልል ለተፈጠረው ሰላምም የምክር ቤቱ አባላት አድናቆታቸውን ገልጸው፤ መንግሥት የዜጎችን በሰላም የመኖር መብት እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምላሻቸው በኢትዮጵያ አሁን ላይ ከቀደመው ጊዜ የተሻለ ሰላም መኖሩን ተናግረዋል፡፡ "የዘላቂ ሰላም ግንባታ እንደ ጦርነት ሁሉ በርካታ ጀግኖችን ይፈልጋል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህ ደግሞ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሰላም ባለቤት በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን የግጭት ነጋዴዎች ዛሬም ቢሆን ሆን ብለውና አቅደው ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ለአብነትም አዲስ አበባን የሁከት ማዕከል ለማድረግ በተቀናጀ አግባብ በርካታ ሙከራዎች መደረጋቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህን በማክሸፍ ረገድ የጸጥታ ተቋማት ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት የተሳካ ሥራ ማከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይ የሚዲያ ነፃነትን ያላግባብ በመጠቀም ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኃን መኖራቸውን ጠቅሰው፤ መንግሥት በመሰል ተቋማት ላይ የሚወስደውን ሕጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ በተለይም አንዳንድ የአገሪቱን መገናኛ ብዙኃን የሟርትና የግጭት ተልዕኮ ይዘው እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሚሰበኩትን የግጭትና የጦርነት ቅስቀሳዎች በመተው ለሰላም ትኩረት ሰጥተን እንስራ ሲሉም ተናግረዋል። "የጦርነት ነጋሪት የሚጎስሙ አካላት አሁንም አሉ" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የሰላም ሁኔታውን ዘላቂና የተሟላ ለማድረግ በመንግሥት በኩል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በየትኛውም አካባቢ ሰላም ለማስፈን መንግሥት ሌት ከቀን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሰላም ሂደት ዘላቂ የሚሆነው በሥራ በመሆኑ የሁሉም የጋራ ጥረት ሊታከልበት ይገባል ብለዋል። የዜጎች የመንቀሳቀስ መብት መገደብ እንደሌለበት ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለጥፋት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን ግን ማስቆም ያስፈልጋል ብለዋል። በመሆኑም የመንቀሳቀስ መብት ለሰላምና ለልማት ካልሆነ በስተቀር ለጥፋት የሚደረግ እንቅስቃሴ በፍጹም ተቀባይነት የለውም፤ ተጠያቂም ያደርጋል ብለዋል። በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮችን በመፍታት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።        
ማስታወቂያ
ፖለቲካ
ሀገራዊ የለውጥ ሂደቱን ማጠናከር እንደሚገባ ምሁራን አመለከቱ
Mar 28, 2023 29
ድሬደዋ መጋቢት 19 /2015(ኢዜአ) ፡- በየደረጃው ለሚያጋጥሙ ችግሮች የተቀናጀ መፍትሔ በመስጠት የተጀመረውን ሀገራዊ የለውጥ ሂደት ማጠናከር እንደሚገባ ምሁራን አመለከቱ። ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲና የተለያዩ ኮሌጆች የተወጣጡ ምሁራን በሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ከድሬዳዋ አስተዳደር አመራሮች ጋር ተወያይተዋል። ምህራኑ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት ፤ መንግስት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከህብረተሰቡ ጋር መወያየቱ ለሚያጋጥሙ ችግሮች የጋራ መፍትሄ ለማምጣት ያግዛል ። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የውጭና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደቻሳ ጋንፉሬ በሰጡት አስተያየት ፤ ባለፉት አራት ዓመታት የመጣው ሀገራዊ ለውጥና ተከትሎም የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሚስተዋሉ የኑሮ ውድነትና የማህበራዊ አገልግሎት ችግሮች ዜጎችን እያማረሩ በመሆናቸው የተቀናጀ መፍትሔ በመስጠት የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። ይህን መሠል ወቅታዊ ውይይት ማስቀጠል ዜጎች የሚሰማቸውን ከማሳወቅ ባሻገር ሁሉም የመፍትሔ አካል እንዲሆን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቁመዋል። መምህር ያሬድ ጥበቡ በበኩላቸው ፤ በለውጡ የተገኙ ሁሉን አቀፍ አበረታች ለውጦችና ውጤቶች ማጠናከር ላይ መረባረብ ይገባል ብለዋል። ለሚያጋጥሙ ችግሮች በተቀናጀ አግባብ መፍትሄ በመስጠት የለውጡን ሂደት ማስቀጠል እንደሚገባ አመልክተዋል። በተለይ በድሬደዋ የሚስተዋለው የኑሮ ውድነትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት መንግስት በአፋጣኝ የመፍትሄ እርምጃ መውሰድ እንዳለበትም ጠቁመዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር በነዳጅ ማደያዎች ውስጥ እየተስፋፋ ለሚገኘው ህገ ወጥና የተበላሸ አሰራር አፋጣኝ መፍትሔ በመስጠት ከትራንስፖርት አገልግሎት ጋር ለተያያዙ ችግሮች መፍትሄ መስጠት እንዳለበት የተናገሩት አቶ ወሰን ቢራቱ ናቸው። የአከባቢው ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል እንዲሁም ለሚስተዋለው የመልካም አስተዳደር ችግሮች የመፍትሔ አካል በመሆን የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል ። ውይይቱን ከመሩት መካከል የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፤ በድሬዳዋ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስና የለወጥ ሂደቱን ለማፅናት ጥናትን መሠረት ያደረገ የተቀናጀ ሁሉንአቀፍ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህን ተግባራት ከዳር ለማድረስ መሰል ውይይቶች በማስፋት ምሁራን ጨምሮ የሌሎችንም የህብረተሰብ ክፍሎችን ድጋፍና ተሳትፎ እንዲጠናከር ይሰራል ብለዋል። በተመሣሣይ በአስተዳደሩ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች ፣ዑጋዞችና አባገዳዎች እንዲሁም የንግዱ ማህበረሰብና ባለሃብቶች የተሳተፉበት ውይይቶች በሌሎች መድረኮች ተካሂደዋል ።  
ኢትዮጵያና ላቲቪያ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በትብብር ለመስራት ተስማሙ
Mar 28, 2023 34
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና ላቲቪያ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በትብብር ለመስራት መስማማታቸው ተገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና አሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ከላቲቪያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስተር የፖለቲካ ዳይሬክተር ቢሮ ረዳት ዋና ፀሐፊ አንዜጂስ ቫይሉምሰንስ ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ አገራት በሁለትዮሽና በባለ ብዙ ወገን የትብብር መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ማጠናከር ላይ ያተኮረ መሆኑን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ አመልክቷል። አምባሳደር እሸቴ ለቫይሉምሰንስ ስለ ሰላም ሂደቱ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። “ላቲቪያ በአውሮፓ ሕብረትና ባልቲክ ባህር ቀጠና ወሳኝ ሚና የምትወጣ አገር ናት” ብለዋል። ኢትዮጵያና ላቲቪያ ያላቸውን ግንኙነት ለማሳደግ ተቀራርበው መስራት እንደሚኖርባቸውም ነው አምባሳደሩ ያመለከቱት። ሁለቱ አገራት በውሃ ሀብት አስተዳደር፣ በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት፣ በትምህርት፣ በኢንፎርሜሽና ኮምዩኒኬሽን ቴክኖሎሎጂ፣ በግብርና፣ በቱሪዝምና በሌሎች ቁልፍ የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል፣ ሰላምና ደህንነት፣ በስደተኞችና ሌሎች የጋራ ጠቀሜታ ባላቸው ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ በቅርበት ለመስራት ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያና ላቲቪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ2008 ነው።
በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ግጭቶችን በመከላከል ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በጋራ መሥራት ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ 
Mar 28, 2023 67
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉ ግጭቶችን በመከላከል ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በጋራ መሥራት እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ። በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የምክር ቤት አባላት ላነሱት ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ምላሽ ሰጥተዋል። በዚህም በምዕራብ ወለጋ አካባቢ የሸኔ ታጣቂ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በሰላም ለመፍታት መንግሥት የሄደበትን እርቀት በተመለከተ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ ባለፉት አምስት ዓመታት በወለጋ አካባቢ የተፈጠረው የሰላም እጦት የልማት ሥራዎችን ለመሥራት እንቅፋት ከመሆን ባለፈ ለሰዎች መሞት፣ መፈናቀልና መሰደድ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል። በአካባቢው የተፈጠረውን የሰላም እጦት ወደ ነበረበት ለመመለስ መንግሥት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው በመግለጽ፤ ለዚህ ይረዳ ዘንድ የሰላም ኮሚቴ በማቋቋም እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ችግሩን ለመፍታት ባለፉት ሁለት ወራት በመንግሥት በኩል ከአሥር ጊዜ በላይ ሙከራዎች ቢደረጉም በአካባቢው የሚንቀሳቀሱት ታጣቂ ኃይሎች አሰላለፍ የተበታተነ በመሆኑ ሂደቱን አዳጋች እንዳደረገው ጠቁመዋል። "ሰላምን የሚጠላ ኃይል የለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለስኬቱ አበክረን እንሰራለን በማለት የመንግሥትን አቋም ግልጽ አድርገዋል። ነገር ግን ለሰላም ከሚደረገው ጥረት ጎን ለጎን የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች የአካባቢውን ሰላም ለማስከበር የተጠናከረ ሥራ እየሰሩ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል። "መገዳደል ለማንም አይጠቅምም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ችግሮችን በውይይት መፍታት ጠቃሚ ነው ብለዋል። የሰላም ሂደቱን በተመለከተ ውጤቱን በጋራ የምናየው ይሆናል ሲሉም ተናግረዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት መቆሙ አንድ እርምጃ ወደፊት ወስዶናል፤ ነገር ግን ወደተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራዎች ይጠብቁናል በማለት ገልጸዋል። ግጭቶች የአገሪቱን ዕድገት ወደ ኋላ እየጎተቱ በመሆኑ ለሰላም መስፈን በጋራ መሥራት አለብን ሲሉ አሳስበዋል።        
ድንበር አካባቢ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሠላማዊ መንገድ በንግግር መፍታት ኢትዮጵያ ቅድሚያ የምትሰጠው ጉዳይ ነው--ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ
Mar 28, 2023 64
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ ድንበር አካባቢ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሠላማዊ መንገድ በንግግር መፍታት ኢትዮጵያ ቅድሚያ የምትሰጠው ጉዳይ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተለያዩ ጉዳዮች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ። ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል አንዱ ኢትዮጵያ ከሱዳንና ደቡብ ሱዳን ከምትዋሰንበት ድንበሮች ጋር በተያያዘ ያጋጠሙ ችግሮችን የተመለከተ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ ድንበር አካባቢዎች ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ለውይይትና ሠላማዊ መንገድ ቅድሚያ መሰጠቱን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር በሚያዋስናት ድንበር ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት ኮሚሽን ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። ከሱዳን ጋር ያለው ችግር በዘላቂነት የሚፈታው ድንበር የማካለሉ ጉዳይ እልባት ሲያገኝ መሆኑን ገልጸው እስከዛው ግለሰቦችና አርሶ አደሮች እንዳይጉላሉ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ጎን ለጎንም "የደቡብ ሱዳን መንግሥት ኢትዮጵያን ወሯል በሚል የሚነሳው አገላለጽ ትክክል አይደለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የደቡብ ሱዳን አርሶና አርብቶ አደሮች ድርቅ ገጥሞናል በሚል 20ሺህ ያህል ከብቶችን ነድተው ወደ ኢትዮጵያ ድንበር አልፈው መግባታቸውን አንስተዋል። ይህንንም በተመለከተ "ከአርሶና አርብቶ አደሩ ጋር ንግግር ተደርጓል፤ የሚያሰጋ ነገር አይፈጠርም" ሲሉም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ያረጋገጡት። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ ከደቡብ ሱዳን ድንበር ጋር በተያያዘ ያጋጠመውን ችግር በሁለቱ አገራት መካከል ውይይት በማድረግ ችግሩን ለመፍታት ከመግባባት ላይ ተደርሷል።
መንግስት ከየትኛውም ኃይል ጋር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ ነው-- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
Mar 28, 2023 49
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦መንግስት ከየትኛውም ኃይል ጋር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት በ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የስድስት ወራት ሪፖርት አስመልክቶ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ኦነግ ሸኔን በሚመለከት ባለፉት ጊዜያት ከአስር ጊዜ በላይ ንግግሮች መደረጉን ገልጸዋል። “የሰላም ጥሪውን በሚመለከት የኦሮሚያ ክልል የተጀመረ ሳይሆን እንደ ፓርቲ ተነጋግረን ነው የወሰነው፤የሰላም ጥሪው የዚሁ ንግግር ተቀጥያ ነው።” ብለዋል። ነገር ግን ቡድኑ አንድ የተሰባሰበ ኃይል አለመሆኑ ችግር መፍጠሩን አመልክተዋል። መንግስት ያለውን ችግር በሰላማዊ መንገድ እና በውይይት ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሁንና ይበልጥ የሰው ነፍስ እንዳይጠፋ ለመከላከል የጸጥታ ኃይሉ ጠንካራ ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። “መንግስት ከየትኛውም ኃይል ጋር ችግሮችን መፍታት የሚፈልገው በውይይትና በንግግር ብቻ ነው” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ወደ ተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
Mar 28, 2023 63
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ወደ ተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እየሰጡ ነው። ዛሬ እየተካሔደ በሚገኘው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛው መደበኛ ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት አሁን ላይ ሰላምን በተመለከተ ከዛሬ ስድስት ወር የተሻለ ሁኔታ አለ ብለዋል።   ወደተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገር ግን አንድ ርምጃ ወደፊት የወሰደ ሥራ ተሠርቷል ሲሉም ገልጸዋል። ባለፉት 50 እና 60 ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው ፖለቲካ የመተላለፍ፣ የሴራ እና የጉልበት ፖለቲካ እንደነበረ ገልጸው “ሰላም አስፈላጊ ነው ብለን በጽኑ እናምናለን፣ ሰላም እንደጦርነት ጀግንነት ይፈልጋል፣ ከጦርነት ያልተናነሰ ሥራ ድካም ይጠይቃል” ብለዋል። የረጋ ሰላማዊ ነገር እንዲሁ አይመጣም አዎንታዊ ሰላም በሀይል አይመጣም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምንጊዜም ሰላም ሲባል የአንድ ሰው ህይወት ማትረፍም ስለሆነ በዚህ ላይ መሥራት ይገባናል ብለዋል።
የሚዲያ ነፃነትን ያላግባብ በመጠቀም ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኃን ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Mar 28, 2023 66
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ የሚዲያ ነፃነትን ያላግባብ በመጠቀም ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኃን ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ፡፡ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የምክር ቤት አባላት በተለይም በአገሪቷ የተለያዩ አካባቢዎች የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ላይ ትኩረት በማድረግ ጥያቄዎችን አንስተዋል። በትግራይ ክልል ለተፈጠረው ሰላምም የምክር ቤቱ አባላት አድናቆታቸውን ገልጸው፤ መንግሥት የዜጎችን በሰላም የመኖር መብት እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምላሻቸው በኢትዮጵያ አሁን ላይ ከቀደመው ጊዜ የተሻለ ሰላም መኖሩን ተናግረዋል፡፡ "የዘላቂ ሰላም ግንባታ እንደ ጦርነት ሁሉ በርካታ ጀግኖችን ይፈልጋል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህ ደግሞ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሰላም ባለቤት በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን የግጭት ነጋዴዎች ዛሬም ቢሆን ሆን ብለውና አቅደው ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ለአብነትም አዲስ አበባን የሁከት ማዕከል ለማድረግ በተቀናጀ አግባብ በርካታ ሙከራዎች መደረጋቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህን በማክሸፍ ረገድ የጸጥታ ተቋማት ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት የተሳካ ሥራ ማከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይ የሚዲያ ነፃነትን ያላግባብ በመጠቀም ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኃን መኖራቸውን ጠቅሰው፤ መንግሥት በመሰል ተቋማት ላይ የሚወስደውን ሕጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ በተለይም አንዳንድ የአገሪቱን መገናኛ ብዙኃን የሟርትና የግጭት ተልዕኮ ይዘው እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሚሰበኩትን የግጭትና የጦርነት ቅስቀሳዎች በመተው ለሰላም ትኩረት ሰጥተን እንስራ ሲሉም ተናግረዋል። "የጦርነት ነጋሪት የሚጎስሙ አካላት አሁንም አሉ" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የሰላም ሁኔታውን ዘላቂና የተሟላ ለማድረግ በመንግሥት በኩል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በየትኛውም አካባቢ ሰላም ለማስፈን መንግሥት ሌት ከቀን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሰላም ሂደት ዘላቂ የሚሆነው በሥራ በመሆኑ የሁሉም የጋራ ጥረት ሊታከልበት ይገባል ብለዋል። የዜጎች የመንቀሳቀስ መብት መገደብ እንደሌለበት ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለጥፋት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን ግን ማስቆም ያስፈልጋል ብለዋል። በመሆኑም የመንቀሳቀስ መብት ለሰላምና ለልማት ካልሆነ በስተቀር ለጥፋት የሚደረግ እንቅስቃሴ በፍጹም ተቀባይነት የለውም፤ ተጠያቂም ያደርጋል ብለዋል። በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮችን በመፍታት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።        
ፖለቲካ
ሀገራዊ የለውጥ ሂደቱን ማጠናከር እንደሚገባ ምሁራን አመለከቱ
Mar 28, 2023 29
ድሬደዋ መጋቢት 19 /2015(ኢዜአ) ፡- በየደረጃው ለሚያጋጥሙ ችግሮች የተቀናጀ መፍትሔ በመስጠት የተጀመረውን ሀገራዊ የለውጥ ሂደት ማጠናከር እንደሚገባ ምሁራን አመለከቱ። ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲና የተለያዩ ኮሌጆች የተወጣጡ ምሁራን በሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ከድሬዳዋ አስተዳደር አመራሮች ጋር ተወያይተዋል። ምህራኑ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት ፤ መንግስት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከህብረተሰቡ ጋር መወያየቱ ለሚያጋጥሙ ችግሮች የጋራ መፍትሄ ለማምጣት ያግዛል ። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የውጭና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደቻሳ ጋንፉሬ በሰጡት አስተያየት ፤ ባለፉት አራት ዓመታት የመጣው ሀገራዊ ለውጥና ተከትሎም የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሚስተዋሉ የኑሮ ውድነትና የማህበራዊ አገልግሎት ችግሮች ዜጎችን እያማረሩ በመሆናቸው የተቀናጀ መፍትሔ በመስጠት የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። ይህን መሠል ወቅታዊ ውይይት ማስቀጠል ዜጎች የሚሰማቸውን ከማሳወቅ ባሻገር ሁሉም የመፍትሔ አካል እንዲሆን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቁመዋል። መምህር ያሬድ ጥበቡ በበኩላቸው ፤ በለውጡ የተገኙ ሁሉን አቀፍ አበረታች ለውጦችና ውጤቶች ማጠናከር ላይ መረባረብ ይገባል ብለዋል። ለሚያጋጥሙ ችግሮች በተቀናጀ አግባብ መፍትሄ በመስጠት የለውጡን ሂደት ማስቀጠል እንደሚገባ አመልክተዋል። በተለይ በድሬደዋ የሚስተዋለው የኑሮ ውድነትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት መንግስት በአፋጣኝ የመፍትሄ እርምጃ መውሰድ እንዳለበትም ጠቁመዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር በነዳጅ ማደያዎች ውስጥ እየተስፋፋ ለሚገኘው ህገ ወጥና የተበላሸ አሰራር አፋጣኝ መፍትሔ በመስጠት ከትራንስፖርት አገልግሎት ጋር ለተያያዙ ችግሮች መፍትሄ መስጠት እንዳለበት የተናገሩት አቶ ወሰን ቢራቱ ናቸው። የአከባቢው ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል እንዲሁም ለሚስተዋለው የመልካም አስተዳደር ችግሮች የመፍትሔ አካል በመሆን የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል ። ውይይቱን ከመሩት መካከል የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፤ በድሬዳዋ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስና የለወጥ ሂደቱን ለማፅናት ጥናትን መሠረት ያደረገ የተቀናጀ ሁሉንአቀፍ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህን ተግባራት ከዳር ለማድረስ መሰል ውይይቶች በማስፋት ምሁራን ጨምሮ የሌሎችንም የህብረተሰብ ክፍሎችን ድጋፍና ተሳትፎ እንዲጠናከር ይሰራል ብለዋል። በተመሣሣይ በአስተዳደሩ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች ፣ዑጋዞችና አባገዳዎች እንዲሁም የንግዱ ማህበረሰብና ባለሃብቶች የተሳተፉበት ውይይቶች በሌሎች መድረኮች ተካሂደዋል ።  
ኢትዮጵያና ላቲቪያ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በትብብር ለመስራት ተስማሙ
Mar 28, 2023 34
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና ላቲቪያ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በትብብር ለመስራት መስማማታቸው ተገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና አሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ከላቲቪያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስተር የፖለቲካ ዳይሬክተር ቢሮ ረዳት ዋና ፀሐፊ አንዜጂስ ቫይሉምሰንስ ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ አገራት በሁለትዮሽና በባለ ብዙ ወገን የትብብር መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ማጠናከር ላይ ያተኮረ መሆኑን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ አመልክቷል። አምባሳደር እሸቴ ለቫይሉምሰንስ ስለ ሰላም ሂደቱ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። “ላቲቪያ በአውሮፓ ሕብረትና ባልቲክ ባህር ቀጠና ወሳኝ ሚና የምትወጣ አገር ናት” ብለዋል። ኢትዮጵያና ላቲቪያ ያላቸውን ግንኙነት ለማሳደግ ተቀራርበው መስራት እንደሚኖርባቸውም ነው አምባሳደሩ ያመለከቱት። ሁለቱ አገራት በውሃ ሀብት አስተዳደር፣ በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት፣ በትምህርት፣ በኢንፎርሜሽና ኮምዩኒኬሽን ቴክኖሎሎጂ፣ በግብርና፣ በቱሪዝምና በሌሎች ቁልፍ የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል፣ ሰላምና ደህንነት፣ በስደተኞችና ሌሎች የጋራ ጠቀሜታ ባላቸው ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ በቅርበት ለመስራት ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያና ላቲቪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ2008 ነው።
በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ግጭቶችን በመከላከል ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በጋራ መሥራት ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ 
Mar 28, 2023 67
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉ ግጭቶችን በመከላከል ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በጋራ መሥራት እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ። በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የምክር ቤት አባላት ላነሱት ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ምላሽ ሰጥተዋል። በዚህም በምዕራብ ወለጋ አካባቢ የሸኔ ታጣቂ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በሰላም ለመፍታት መንግሥት የሄደበትን እርቀት በተመለከተ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ ባለፉት አምስት ዓመታት በወለጋ አካባቢ የተፈጠረው የሰላም እጦት የልማት ሥራዎችን ለመሥራት እንቅፋት ከመሆን ባለፈ ለሰዎች መሞት፣ መፈናቀልና መሰደድ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል። በአካባቢው የተፈጠረውን የሰላም እጦት ወደ ነበረበት ለመመለስ መንግሥት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው በመግለጽ፤ ለዚህ ይረዳ ዘንድ የሰላም ኮሚቴ በማቋቋም እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ችግሩን ለመፍታት ባለፉት ሁለት ወራት በመንግሥት በኩል ከአሥር ጊዜ በላይ ሙከራዎች ቢደረጉም በአካባቢው የሚንቀሳቀሱት ታጣቂ ኃይሎች አሰላለፍ የተበታተነ በመሆኑ ሂደቱን አዳጋች እንዳደረገው ጠቁመዋል። "ሰላምን የሚጠላ ኃይል የለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለስኬቱ አበክረን እንሰራለን በማለት የመንግሥትን አቋም ግልጽ አድርገዋል። ነገር ግን ለሰላም ከሚደረገው ጥረት ጎን ለጎን የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች የአካባቢውን ሰላም ለማስከበር የተጠናከረ ሥራ እየሰሩ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል። "መገዳደል ለማንም አይጠቅምም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ችግሮችን በውይይት መፍታት ጠቃሚ ነው ብለዋል። የሰላም ሂደቱን በተመለከተ ውጤቱን በጋራ የምናየው ይሆናል ሲሉም ተናግረዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት መቆሙ አንድ እርምጃ ወደፊት ወስዶናል፤ ነገር ግን ወደተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራዎች ይጠብቁናል በማለት ገልጸዋል። ግጭቶች የአገሪቱን ዕድገት ወደ ኋላ እየጎተቱ በመሆኑ ለሰላም መስፈን በጋራ መሥራት አለብን ሲሉ አሳስበዋል።        
ድንበር አካባቢ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሠላማዊ መንገድ በንግግር መፍታት ኢትዮጵያ ቅድሚያ የምትሰጠው ጉዳይ ነው--ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ
Mar 28, 2023 64
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ ድንበር አካባቢ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሠላማዊ መንገድ በንግግር መፍታት ኢትዮጵያ ቅድሚያ የምትሰጠው ጉዳይ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተለያዩ ጉዳዮች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ። ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል አንዱ ኢትዮጵያ ከሱዳንና ደቡብ ሱዳን ከምትዋሰንበት ድንበሮች ጋር በተያያዘ ያጋጠሙ ችግሮችን የተመለከተ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ ድንበር አካባቢዎች ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ለውይይትና ሠላማዊ መንገድ ቅድሚያ መሰጠቱን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር በሚያዋስናት ድንበር ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት ኮሚሽን ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። ከሱዳን ጋር ያለው ችግር በዘላቂነት የሚፈታው ድንበር የማካለሉ ጉዳይ እልባት ሲያገኝ መሆኑን ገልጸው እስከዛው ግለሰቦችና አርሶ አደሮች እንዳይጉላሉ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ጎን ለጎንም "የደቡብ ሱዳን መንግሥት ኢትዮጵያን ወሯል በሚል የሚነሳው አገላለጽ ትክክል አይደለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የደቡብ ሱዳን አርሶና አርብቶ አደሮች ድርቅ ገጥሞናል በሚል 20ሺህ ያህል ከብቶችን ነድተው ወደ ኢትዮጵያ ድንበር አልፈው መግባታቸውን አንስተዋል። ይህንንም በተመለከተ "ከአርሶና አርብቶ አደሩ ጋር ንግግር ተደርጓል፤ የሚያሰጋ ነገር አይፈጠርም" ሲሉም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ያረጋገጡት። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ ከደቡብ ሱዳን ድንበር ጋር በተያያዘ ያጋጠመውን ችግር በሁለቱ አገራት መካከል ውይይት በማድረግ ችግሩን ለመፍታት ከመግባባት ላይ ተደርሷል።
መንግስት ከየትኛውም ኃይል ጋር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ ነው-- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
Mar 28, 2023 49
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦መንግስት ከየትኛውም ኃይል ጋር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት በ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የስድስት ወራት ሪፖርት አስመልክቶ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ኦነግ ሸኔን በሚመለከት ባለፉት ጊዜያት ከአስር ጊዜ በላይ ንግግሮች መደረጉን ገልጸዋል። “የሰላም ጥሪውን በሚመለከት የኦሮሚያ ክልል የተጀመረ ሳይሆን እንደ ፓርቲ ተነጋግረን ነው የወሰነው፤የሰላም ጥሪው የዚሁ ንግግር ተቀጥያ ነው።” ብለዋል። ነገር ግን ቡድኑ አንድ የተሰባሰበ ኃይል አለመሆኑ ችግር መፍጠሩን አመልክተዋል። መንግስት ያለውን ችግር በሰላማዊ መንገድ እና በውይይት ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሁንና ይበልጥ የሰው ነፍስ እንዳይጠፋ ለመከላከል የጸጥታ ኃይሉ ጠንካራ ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። “መንግስት ከየትኛውም ኃይል ጋር ችግሮችን መፍታት የሚፈልገው በውይይትና በንግግር ብቻ ነው” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ወደ ተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
Mar 28, 2023 63
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ወደ ተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እየሰጡ ነው። ዛሬ እየተካሔደ በሚገኘው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛው መደበኛ ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት አሁን ላይ ሰላምን በተመለከተ ከዛሬ ስድስት ወር የተሻለ ሁኔታ አለ ብለዋል።   ወደተሟላ ሰላም ለመሄድ በርካታ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገር ግን አንድ ርምጃ ወደፊት የወሰደ ሥራ ተሠርቷል ሲሉም ገልጸዋል። ባለፉት 50 እና 60 ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው ፖለቲካ የመተላለፍ፣ የሴራ እና የጉልበት ፖለቲካ እንደነበረ ገልጸው “ሰላም አስፈላጊ ነው ብለን በጽኑ እናምናለን፣ ሰላም እንደጦርነት ጀግንነት ይፈልጋል፣ ከጦርነት ያልተናነሰ ሥራ ድካም ይጠይቃል” ብለዋል። የረጋ ሰላማዊ ነገር እንዲሁ አይመጣም አዎንታዊ ሰላም በሀይል አይመጣም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምንጊዜም ሰላም ሲባል የአንድ ሰው ህይወት ማትረፍም ስለሆነ በዚህ ላይ መሥራት ይገባናል ብለዋል።
የሚዲያ ነፃነትን ያላግባብ በመጠቀም ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኃን ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Mar 28, 2023 66
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ የሚዲያ ነፃነትን ያላግባብ በመጠቀም ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኃን ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ፡፡ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የምክር ቤት አባላት በተለይም በአገሪቷ የተለያዩ አካባቢዎች የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ላይ ትኩረት በማድረግ ጥያቄዎችን አንስተዋል። በትግራይ ክልል ለተፈጠረው ሰላምም የምክር ቤቱ አባላት አድናቆታቸውን ገልጸው፤ መንግሥት የዜጎችን በሰላም የመኖር መብት እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምላሻቸው በኢትዮጵያ አሁን ላይ ከቀደመው ጊዜ የተሻለ ሰላም መኖሩን ተናግረዋል፡፡ "የዘላቂ ሰላም ግንባታ እንደ ጦርነት ሁሉ በርካታ ጀግኖችን ይፈልጋል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህ ደግሞ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሰላም ባለቤት በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን የግጭት ነጋዴዎች ዛሬም ቢሆን ሆን ብለውና አቅደው ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ለአብነትም አዲስ አበባን የሁከት ማዕከል ለማድረግ በተቀናጀ አግባብ በርካታ ሙከራዎች መደረጋቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህን በማክሸፍ ረገድ የጸጥታ ተቋማት ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት የተሳካ ሥራ ማከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይ የሚዲያ ነፃነትን ያላግባብ በመጠቀም ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኃን መኖራቸውን ጠቅሰው፤ መንግሥት በመሰል ተቋማት ላይ የሚወስደውን ሕጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ በተለይም አንዳንድ የአገሪቱን መገናኛ ብዙኃን የሟርትና የግጭት ተልዕኮ ይዘው እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሚሰበኩትን የግጭትና የጦርነት ቅስቀሳዎች በመተው ለሰላም ትኩረት ሰጥተን እንስራ ሲሉም ተናግረዋል። "የጦርነት ነጋሪት የሚጎስሙ አካላት አሁንም አሉ" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የሰላም ሁኔታውን ዘላቂና የተሟላ ለማድረግ በመንግሥት በኩል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በየትኛውም አካባቢ ሰላም ለማስፈን መንግሥት ሌት ከቀን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሰላም ሂደት ዘላቂ የሚሆነው በሥራ በመሆኑ የሁሉም የጋራ ጥረት ሊታከልበት ይገባል ብለዋል። የዜጎች የመንቀሳቀስ መብት መገደብ እንደሌለበት ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለጥፋት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን ግን ማስቆም ያስፈልጋል ብለዋል። በመሆኑም የመንቀሳቀስ መብት ለሰላምና ለልማት ካልሆነ በስተቀር ለጥፋት የሚደረግ እንቅስቃሴ በፍጹም ተቀባይነት የለውም፤ ተጠያቂም ያደርጋል ብለዋል። በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮችን በመፍታት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።        
ማህበራዊ
ከኦቲዝም ጋር የሚኖሩ ዜጎችን የትምህርት እድል ተጠቃሚ ለማድረግ የጋራ ርብርብ ይጠይቃል
Mar 28, 2023 29
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ) ከኦቲዝም ጋር የሚኖሩ ዜጎችን የትምህርት እድል ተጠቃሚ በማድረግ ይበልጥ አምራች ዜጋ እንዲሆኑ ሁሉም አካላት በትብብር እንዲሰሩ በጉዳዩ ላይ የሚሰሩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጠየቁ። ኒያ ፋውንዴሽን፣ ነህሚያ ኦቲዝም ማዕከል፣ ብራይት ኦቲዝም ማዕከል ሃዋሳ፣ ቤቴል አዳማ ኦቲዝም ማዕከልና ምሉዕ ፋውንዴሽን በጋራ በመሆን በኢትዮጵያ በኦቲዝም የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በአሳሳቢ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል። በኒያ ፋውንዴሽን የጆይ ኦቲዝም ማዕከል ዋና ሥራ አስኪያጅ እሌኒ ዳምጠው በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ የኦቲዝም እክል ብዙም ትኩረት ባለመሰጠቱ በቤተሰቦቻቸውና በማኅበረሰቡ ብዙ እንግልት እየደረሰባቸው ይገኛሉ። በተለይ ደግሞ የአገሪቱ የትምህርት ሥርዓት ከኦቲዝም ጋር ለሚኖሩ ዜጎች በቂ የሆነ እድል የሚሰጥ አይደለም ብለዋል። በዚህም ምክንያት ከራሳቸው አልፈው ለአገርና ቤተሰብ አለኝታ መሆን የሚችሉ በርካታ ዜጎች ባክነው ይቀራሉ ነው ያሉት። ይህን ችግር መነሻ በማድረግ ጆይ ኦቲዝም ማዕከል አስራ ሁለት ልጆችን አስተምሮ በማብቃት በግቢው ውስጥ ሥራ እንዲይዙ አደርጓል ብለዋል። በዚህም እነዚህ ዜጎች የራሳቸውን ህይወት ከመደጎም ባለፈ ከደሞዛቸው ተቆራጭ እየሆነ ለመንግሥት ግብር ማስገባት መጀመራቸውን ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅትም 80 ልጆችን በማቀፍ የማስተማርና የመንከባከብ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አመላክተዋል።   በመሆኑም የኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ከኦቲዝም ጋር የሚኖሩ ዜጎችን ታሳቢ ያደረገ መሆን እንደሚገባው ነው ያመላከቱት። የነህሚያ ኦቲዝም ማዕከል ዋና ሥራ አስኪያጅ ራሔል አባይነህ በበኩላቸው እነዚህ ልጆች ድጋፍና ትምህርት ከተሰጣቸው እንደማንኛውም ሰው አምራች ዜጋ መሆን እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ዜጎቹ በተለይም በትምህርት ሥርዓት ውስጥ የሚካተቱበትን ሁኔታ ለማጠናከር መስራት ይገባል ብለዋል። ብራይት ኦቲዝም ማዕከል ሃዋሳ ዋና ሥራ አስኪያጅ ትዕግስት አበበ በበኩላቸው ተቋማቸው እነዚህ ዜጎች ከኢኮኖሚ ጥገኝነት እንዲወጡ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የትምህርት እድል እንዲሰጣቸው በማድረግ ራሳቸውን እንዲችሉ ሁሉም ሊተባበር ይገባዋል ነው ያሉት። የቤቴል አዳማ ኦቲዝም ማዕከል ሥራ አስኪያጅ ገነት ንጉሴና የምሉዕ ፋውንዴሽን ኦቲዝም ማዕከል ዋና ሥራ አስኪያጅ ትዕግስት ሃይሉ በበኩላቸው፤ ማዕከላቸው በኦቲዝም የተያዙ ልጆችን በማሰባሰብ የህይወት ክህሎት ሥልጠና እየሰጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። እነዚህ ዜጎች ራሳቸውን ብቁ ለማድረግ የሚያስችላቸውን ድጋፎች እንዲያገኙ መሥራት የሁሉም ሃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል። አምስቱ የኦቲዝም ማዕከላት የኦቲዝምን ችግር ያለባቸውን ዜጎች መብት ለማስከበርና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል የኢትዮጵያ ኦቲዝም ሶሳይቲን ለመመሥረት መግባባት ላይ ደርሰዋል። በቀጣይም ሌሎች በመስኩ የተሰማሩ ተቋማትን እያካተቱ እንደሚሔዱ ተናግረዋል።  
የሕዝቦችን ሁለንተናዊ ትስስር ለማጠናከር እንሰራለን - የኦሮሚያና የሶማሌ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳደሮች  
Mar 28, 2023 35
ጅግጅጋ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ) ጅግጅጋ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ) ፡- በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች ሕዝቦች መካከል የቆየውን ሁለንተናዊ ትስስር በልማት ለማጠናከር እንደሚሰሩ የክልሎች ርዕሳነ መስተዳደሮች ገለጹ። ርዕሳነ መስተዳደሮቹ ይህንን የገለጹት፤ የኦሮሚያ ክልል በመደበው 40 ሚሊዮን ብር ውጪ በጅግጅጋ ከተማ የተገነባ "ካህ" ተብሎ የተሰየመውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዛሬ በጋራ ሲመርቁ ነው።   የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ በጅግጅጋ ከተማ የተገነባው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሁለቱን ክልሎች ህዝቦች በልማት ለማስተሳሰር ከተከናወኑ ስራዎች አንዱ ማሳያ ነው። አቶ ሽመልስ "የሁለቱን ሕዝቦች የቆየ ትስስር ለማጠናከርና በልማት ለማስተሳሰር ያስገነባነው ይህ ትምህርት ቤት በቀጣይ አገርን የሚመሩ ወጣት ምሁራን የሚወጡበት ይሆናል" ብለዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድ በበኩላቸው፤ "የኦሮሚያ ክልል ያስገነባው ትምህርት ቤት ከወንድም ሕዝብ የተደረገልን ትልቅ ስጦታ ነው" ብለዋል። "የሁለቱ ሕዝቦች ያላቸው ሁለንተናዊ ትስስር በልማት ለመደገፍና በጋራ ለማደግ የያዙትን ጥረት ስኬታማ መሆኑን ይህ ትምህርት ቤት በማሳያነት የሚጠቀስ ነው" ሲሉም ገልጸዋል። ትምህርት ቤቱ የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች እንዲማሩበት ይሰራል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ትምህርት ቤቱን ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ጋር ለማስተሳሰር መታቀዱንም ጠቁመዋል። ባለ ሁለት ወለል ሕንጻ የሆነው ትምህርት ቤት የመማሪያ ክፍል፣ ቤተ-መጻሕፍት ፣ ቤተ-ሙከራና የአስተዳደር ክፍሎችን ያካተተ ነው። በስነ ስርዓቱ ላይ የሁለቱ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ፣ የጎሳ መሪዎች፣ የኃይማኖት አባቶች ፣ወላጆችና ተማሪዎች፣ ተገኝተዋል።
ሙስናን ለመከላከል በተቋማት መካከል ትብብርና ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር ይሰራል - የፌደራል ሥነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን 
Mar 28, 2023 28
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ) ሙስናን ለመከላከል በተቋማት መካከል ትብብርና ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ የፌደራል ሥነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ገለጸ። ኮሚሽኑ ከ97 የፌደራል ተቋማት ለተውጣጡ ከ270 በላይ የሥራ ኃላፊዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና በቢሸፍቱ እየሰጠ ነው። ሥልጠናው የሙስና ወንጀል፣ ኦዲትና ሙስናን መከላከል፣ በሥነ-ምግባር ስትራቴጂ ዙሪያዎች ላይ ትኩረት አድርጓል ተብሏል።   የፌደራል ሥነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወዶ አጦ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ሙስናን ለመከላከል የተቀናጀ አሰራር መዘርጋትና ማጠናከር ወሳኝ ነው። በተናጠል የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ውጤት አለማምጣታቸውን ገልጸው ይህንን ክፍተት ለመሙላት የተቀናጀ አሰራር መጠናከር አለበት ብለዋል። በመሆኑም በተቋማት መካከል ያለው ቅንጅታዊ አሰራር ከተጠናከረ በአገር አቀፍ ደረጃ ሙስናን ለመከላከል የተጀመረው ጥረት ፍሬያማ እንደሚሆን ገልጸዋል። በአገሪቱ ማኅበራዊ ቀውስን በማስፋፋት ጉልህ ድርሻ የሚጫወተውን ሙስናን ሥነ-ምግባር ችግሮች ሊቀንሱ የሚችሉት በኅብረተሰቡ ተሳትፎ ጭምር መሆኑንም አስገንዝበዋል። ለሦስት ቀናት በሚቆየው በዚሁ ሥልጠና ከተቋማቱ የተውጣጡ የፀረ ሙስናና ሥነ-ምግባር ዳይሬክተሮች፣ የኦዲት ኃላፊዎች፣ የለውጥ አመራሮችና የሕግ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።    
ፋብሪካው የሚያቀርበው ዳቦ በዋጋም ሆነ በጥራት የህብረተሰቡን አቅምና ፍላጎት ያገናዘበ ነው- ተጠቃሚዎች
Mar 28, 2023 32
ጎንደር፤ 19 ቀን 2015(ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ በቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ተገንብቶ በቅርቡ ሥራ የጀመረው የዱቄትና ዳቦ ፋብሪካ የሚያቀርበው ዳቦ በዋጋም ሆነ በመጠን የህብረተሰቡን አቅም ያገናዘበ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተጠቃሚዎች ተናገሩ፡፡ በከተማው ዳቦ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ 15 የዳቦ መሸጫ ሱቆች ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ አስታውቀዋል። በከተማው የቀበሌ 09 ነዋሪው አቶ ካሳሁን ምትኩ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በፋብሪካው የሚመረተው ዳቦ በመጠንም ሆነ በዋጋ እሳቸውን ጨምሮ ሌላውንም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኝ የህብረተሰብ ክፍል አቅምን ያገናዘበ በመሆኑ ተመራጭ ነው። አንድ ዳቦ ከግል የዳቦ መሸጫ ሱቅ ከስምንት እስከ ሰባት ብር እየገዙ ሲጠቀሙ መቆየታቸውን ያስታወሱት አስተያየት ሰጪው፤ አሁን በፋብሪካ የሚቀርበው ዳቦ የሦስት ብር ቅናሽ እንዳለው ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል፡፡ ሌላው የከተማው ነዋሪ ወጣት አዲሱ እሸቴ ፤ በአካባቢው የዳቦ ዋጋ በየጊዜው ጭማሪ የሚያሳይ ከመሆኑም በላይ፤ ፋብሪካው የሚያቀርበው ዳቦ በመጠንም ሆነ በጥራት የተጠቃሚውን ፍላጎት እንደማያሟላ ገልጿል፡፡ በፋብሪካው የሚመረተውን ዳቦ ከግል ዳቦ መሸጫ ሱቆች በዋጋና በመጠን የተሻለ በመሆኑ በአራት ብር ሂሳብ በመግዛት እየተጠቀመ እንደሆነ ተናግሯል። በግል ዳቦ ቤቶች በመጠን ያነሰና አንዱ ዳቦ ስምንት ብር እንደሚሸጥ ጠቁሟል፡፡ ከግል ዳቦ ቤቶች የሚሸጠው ዳቦ መጠኑ አነስተኛ ከመሆኑም በላይ ዋጋውም የተጋነነ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በከተማው የቀበሌ 03 ነዋሪ ወይዘሮ ሙሉ ጀንበር ናቸው፡፡ በፋብሪካው እየቀረበ ያለው ዳቦ የዋጋ ቅናሽ ያለው ፤ ክብደቱም ሆነ ጥራቱ ተመራጭ በመሆኑም ስርጭቱ በሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡ በከተማው የቀበሌ 05 ነዋሪ ወይዘሪት እናት ማሪቱ ፤ በከተማዋ የዳቦ መሸጫ ሱቆች መከፈታቸው የሥራ እድል እንደፈጠረላቸው ተናግራለች። የጎንደር ዳቦና ዱቄት ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ አቶ መስፍን አለምነው በበኩላቸው ፤ፋብሪካው የሚያመርተውን ዳቦ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ 15 መሸጫ ሱቆች መቋቋማቸውን አስታውቀዋል። የአንዱ ዳቦ ክብደት 100 ግራም እንዲሆንና በአራት ብር ሂሳብ እንዲሸጥ የአሠራር ሥርዓት ተዘርግቶ ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል፡፡ በገቢና በኑሮ ዝቅተኛ የሆነውን የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ የተቋቋመው ፋብሪካ በቀጣይ የዳቦ ስርጭቱ ባልተዳረሰባቸው የከተማው ክፍሎች፣ አጎራባች ወረዳዎችና ሌሎች ከተሞች ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል፡፡ ፋብሪካው 40 ለሚደርሱ ሥራ ፈላጊዎች የሥራ እድል መፍጠሩን የተናገሩት አቶ መስፍን፤ በሙሉ አቅሙ ወደ ማምረት ሲሸጋገር በቀን 300 ሺህ ዳቦ የማምረት አቅም አለው ብለዋል፡፡ በቀን 450 ኩንታል የስንዴ ዱቄት የማምረት አቅም ያለው የዱቁት ፋብሪካው ከዳቦ ማምረቻው ጋር አብሮ እንደተቋቋመ አውሰተው፤ ፋብሪካው የስንዴ ግብዓት ከገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን እየቀረበለት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የጎንደር ዳቦና ዱቄት ፋብሪካ በቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት በ100 ሚሊዮን ብር ወጪ የተቋቋመ ሲሆን፣ ባለፈው ወር በቀዳማዊት ዝናሽ ታያቸው ተመርቆ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል።  
ኢኮኖሚ
ኢትዮጵያና ጃፓን በሆርቲካልቸር ልማት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ
Mar 28, 2023 27
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያና ጃፓን በሆርቲካልቸር ልማት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ የአነስተኛ አርሶ አደሮችን የሆርቲካልቸር አቅም ማጎልበቻ ፕሮጀክት ሁለተኛ ምዕራፍ ተፈጻሚ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል። የግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር መለሰ መኮንንና የጃፓን አለም አቀፍ የልማት ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የኢትዮጵያ ተወካይ ሞሪሃራ ካሱኪ ስምምነቱን ተፈራርመዋል። አነስተኛ አርሶ አደሮች የሆርቲካልቸር አቅም ማጎልበቻ ፕሮጀክት በምዕራፍ አንድ አማራ እና ኦሮሚያ ክልል ሲተገበር መቆየቱ ተገልጿል። በስምምነቱ መሰረት የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ምዕራፍ በደቡብና ሲዳማ ክልሎች እንደሚተገበር ተጠቁሟል። ሚኒስትር ዲኤታው ዶክተር መለሰ መኮንን የጃፓን መንግስት ሆርቲካልቸር ልማት ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ለመስራት ያለውን ፍላጎት አድንቀዋል፡፡ የጃፓን አለም አቀፍ የልማት ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የኢትዮጵያ ተወካይ ሞሪሃራ ካሱኪ በፕሮጀክቱ በምዕራፍ አንድ የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። በምዕራፍ ሁለት የፕሮጀክቱ ትግበራ ጃይካ ለአነስተኛ አርሶ ደሮች በሆርቲካልቸር ልማት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለጻቸውን ከግብርና ሚኒስቴር ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ግብርና ኤክስቴንሽን የምክክር አገልግሎት ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ 
Mar 28, 2023 30
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ) የኢትዮጵያ የዲጂታል ግብርና ኤክስቴንሽን የምክክር አገልግሎት ፍኖተ ካርታ ዛሬ ይፋ ሆኗል። የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢኒስቲትዩት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ፍኖተ ካርታ ለቀጣይ ሰባት ዓመታት ስራ ላይ እንደሚውል ተገልጿል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ማንደፍሮ ንጉሴ እንዳሉት፤ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና የኤክስቴንሽን አገልግሎት መጠናከር አለበት። በተለይም ደግሞ የተቀናጀ የዲጂታል ኤክስቴንሽን አገልግሎት ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑንና ይህን ታሳቢ ያደረገ ፍኖተ ካርታው መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ፍኖተ ካርታው የኤክስቴንሽን አገልግሎቱን በወጥነት ለመምራት እንደሚያስችልና በተለያዩ ተቋማት የሚሰራውን የግብርና ዲጂታል ኤክስቴንሽን አገልግሎት ለማቀናጀት እንደሚያግዝ ተናግረዋል። በፍኖተ ካርታው አማካኝነት የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን አማራጮችና ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም ወቅታዊ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና ምክር ለአርሶና አርብቶ አደሩ ይሰጣል ነው ያሉት። አርሶ አደሩ የምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያና የፀረ አረም ኬሚካልን በመጠቀም አርሶ አደሩ ገበያ ተኮር ምርት እንዲያመርት የሚያስችሉ የመረጃ ልውውጥ ይደረጋል ብለዋል። ፍኖተ ካርታው የግብርና ኤክስቴንሽን የምክር አገልግሎት ዘመናዊ በማድረግ በቂ መረጃ ለአርሶ አደሩ በመስጠት ምርትና ምርታነትን ለማሳደግ ያስችላል ያሉት ደግሞ የግብርና ሚንስትር ዴኤታ ዶክተር መለሰ መኮንን ናቸው። የግብርናውን ዘርፍ አሁን ካለበት በማዘመን በአገር ደረጃ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በሁሉም የግብርና ዘርፎች እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አርሶ አደሩን በእውቅትና በክህሎት በማብቃት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ዛሬ ይፋ የሆነው ፍኖተ ካርታም የዚህ ጥረት አንዱ ማሳያ መሆኑን አመልክተዋል።          
በአፍሪካ የኢነርጂ ዘርፍ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ የመንግስትና የግሉን ዘርፍ አጋርነት ማጠናከር እንደሚገባ ተጠቆመ
Mar 28, 2023 23
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ):- በአፍሪካ የኢነርጂ ዘርፍ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ የመንግስትና የግሉን ዘርፍ አጋርነት መጠናከር እንዳለበት ተመላከተ። በአፍሪካ የኃይል ልማትና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ዙሪያ የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ በጋራ መስራት በሚችሉት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ጉባኤ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል፡፡ ጉባኤውን የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና በአፍሪካ የኃይል ሽግግር ላይ የሚሰራው ሬስ ፎር አፍሪካ ፋውንዴሽን የጣልያን ተቋም በመተባበር ያዘጋጁት ነው። አፍሪካ በኢነርጂ ዘርፍ ዕምቅ ሃብት ቢኖራትም በዘርፉ ላይ ያሉ በርካታ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል አልተቻለም ተብሏል፡፡ በአፍሪካ ሕብረት እና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የጣሊያን ቋሚ ተወካይ አልቤርቶ በርቶኒ በአፍሪካ የኢነርጂ ዘርፍን ለማሳደግ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ገልጸዋል። በተለይ በኃይል ማመንጨት፣ በኃይል ስርጭት፣ የመሰረተ ልማት ግንባታ እንዲሁም በከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ ላይ መንግስትና የግሉ ዘርፍ ተባብረው መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የፖሊሲና የቁጥጥር ማዕቀፎች ላይ የሚታዩ ችግሮችን በማሻሻልም ለኢነርጂው ዘርፍ ዕድገት መስራት እንደሚገባ ጠቁመው፤ ይህ ካልሆነ ሕዝቡን ከዘርፉ ተጠቃሚ ማድረግ አዳጋች ነው ብለዋል። ጣሊያን በአፍሪካ አገራት የኢነርጂ ዘርፉ ላይ የጀመረችውን በጎ ስራ አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠው ያሉትን ዕድሎች ወደ ሃብት ለመቀየርና ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ዝግጁ መሆኗንም ነው ቋሚ ተወካዩ የተናገሩት። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ፣ በኢትዮጵያ ለኢነርጂ ኢንቨስትመንት መስክ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል፡፡   የኢነርጂ ፖሊሲ ተከልሶ ወደ ትግበራ ለመግባት በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸው፤ ፖሊሲው የግል ዘርፉ ወደ ኢነርጂ ኢንቨስትመንት እንዲሰማራ የሚጋብዝ ነው ብለዋል፡፡ የኢንቨስትመንት አዋጅ መሻሻሉም በኢነርጂ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ለሚሰማሩ የግሉ ክፍል ኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ትልቅ ዕድል መሆኑን አመልክተዋል። በኃይል ልማት እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ዙሪያ የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ በጋራ መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ያተኮረው ይህ ጉባኤም ለኢትዮጵያ ጥሩ አጋጣሚ ነው መሆኑንም ነው ሚኒስትር ዴኤታው ያመለከቱት። የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ መሻሻልም የግሉ ዘርፍ ወደ ኢነርጂ ኢንቨስትመንት እንዲገባ መንገድ የሚከፍት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ አገራት የኤሌትሪክ ኃይል እየሸጠች እንደምትገኝና በኃይል ሽያጭ ምቹ ስትራጂቴካዊ አካባቢ ላይ እንደተቀመጠች አመልክተዋል፡፡ ለሶስት ቀናት በሚቆየው የፖሊሲ ምክክር መድረክ በአፍሪካ የኃይል ልማት ላይ የተሰሩ ጥናቶች ቀርበው በመንግስትና የግል ዘርፍ ኃላፊዎች ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል።  
ኢንተርፕራይዞች በመንግስት ዋስትና ብድር የሚያገኙበት ስርዓት እየተዘጋጀ ነው
Mar 28, 2023 57
አዲስ አበባ መጋቢት 19/2015 (ኢዜአ)፦ኢንተርፕራይዞች በመንግስት ዋስትና ብድር የሚያገኙበት ስርዓት እየተዘጋጀ መሆኑን የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ገለጹ። ኢንተርፕራይዞች ከምሥረታቸው ጀምሮ በእንቅስቃሴ ሂደታቸው የፋይናንስ፣ የመሥሪያና መሸጫ ቦታዎች እንዲሁም የገበያ ትስስር ፈተናዎች እንደሚገጥማቸው በተደጋጋሚ ይነሳል። ኢንተርፕይዞች ሰፍተውና ጎልብተው የሥራ ዕድል እንዳይፈጥሩ የፋይናንስ አቅርቦት ዋነኛ ማነቆ እንደሆነ እንዲሁ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የኢንተርፕራይዞችን የፋይናንስ ክፍተት፣ የብድር ዋስትናና አማራጭ የሕግ ማዕቀፎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሂዷል።   ምክክሩን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፈርስት ኮንሰልትና ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በትብበር የተዘጋጀ ነው። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሡ ጥላሁን በዚሁ ወቅት እንዳሉት የብድር ዋስትና በኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ለሆኑት ለጥቃቅን፣ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ወሳኝ ነው። ኢንተርፕራይዞችን ከተመሠረቱ በኋላም ብድር ለማግኘት በመንግሥት ዋስትና ከአበዳሪ ተቋማት ብድር የሚያገኙበት ሥርዓት እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል። የብድር ዋስትናው የኢንተርፕራይዞች ዕድገት በማረጋግጥ ውጤታማ ስለሚያደርጋቸው በመንግሥት ዋስትና የሚወሰደው ገንዘብ እንደማያከስር ታምኖበታል ብለዋል። የብድርና የመሬት አቅርቦት እንዲሁም የገበያ ትስስር ተግዳሮት በሆነበት ስኬታማ ኢንተርፕራይዞችን ማፍራትና የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ ማድረግ አዳጋች መሆኑን ጠቁመዋል። የብድር ዋስትና ሥርዓት መዘርጋቱ ኢንተርፕራይዞች ብድር ለማግኘት የሚገጥማቸውን የዋስትና ችግር በመፍታት ምርታማ እንደሚያደርጋቸውም ጠቁመዋል። በኢኮኖሚው ውስጥ የተሻለ ሚና እንዲኖራቸውም ያደርጋል ብለዋል። በጥናት በቀረቡ አማራጮች ላይ በቀጣይ ባለሙያዎች፣ አጋር አካላትና የፋይናንስ ተቋማት መክረውበት ከዳበረ በኋላ የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያስገባ የብድር ዋስትና ፈንድ እንደሚቋቋም ገልጸዋል። የፋይናንስ አቅርቦቱና የድጋፍ አገልግሎቱን አጣጥሞ ከተሰራበት የኢንተርፕራይዞች የመክሰም ምጣኔ እየቀነሰ እንደሚሄድ አቶ ንጉሡ አመላክተዋል። ኢንተርፕራይዞቹ ውጤታማ እንዲሆኑና እንዳይከስሩ እንዲሁም አበዳሪ ተቋማትንም ይዘው እንዳይወድቁ መንግሥት በኃላፊነት ብቃታቸውን የማሳደግና አቅማቸውን የማጎልበት ሥራ እንደሚሰራ አስረድተዋል።    
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በማደግ ላይ ያሉ አገሮች ለአካታች ዲጂታል ኢኮኖሚ ትግበራ ትኩረት ሰጥተው ካልሰሩ እኤአ በ2025 ከ1 ትሪሊየን ዶላር በላይ ገቢ ሊያጡ ይችላሉ- ተመድ
Mar 27, 2023 102
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015(ኢዜአ)፦ በማደግ ላይ ያሉ አገሮች ለአካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ትግበራ ትኩረት ሰጥተው ካልሰሩ እኤአ በ2025 ከአገር ውስጥ ዓመታዊ ምርታቸው ከ1 ትሪሊየን ዶላር በላይ ገቢ ሊያጡ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ "የፈጠራና ቴክኖሎጂ ለፆታ እኩልነት" በሚል መሪ ሃሳብ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ውይይት አካሂዷል።   የድርጅቱ የሰብአዊ ጉዳዮች የኢትዮጵያ አስተባባሪ ዶክተር ካትሪን ሶዚ፤ የዲጂታል ዘመን ሥራዎችን ቀላል በማድረግ በተለይም ሴቶችና ህፃናትን ተጠቃሚ ሊያደርጉ የሚችሉ በርካታ ዕድሎችን ይዞ መጥቷል ብለዋል። በዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም ከኢንተርኔት ተደራሽነት ውጭ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ተደራሽነቱን ማስፋት አስፈላጊ ነው ሲሉ ገልጸዋል። አካታች የዲጂታል ስትራቴጂ ተግባራዊ አለማድረግ በማኅበራዊና የምጣኔ ሃብት እድገት ላይ ተጽዕኖው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፤ አገሮች በቀጣይ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል ነው ያሉት። አፍሪካን ጨምሮ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው አገሮች ባለፉት አሥርት ዓመታት ለአካታች ኢንተርኔት ትኩረት ባለመስጠታቸው ከዓመታዊ የአገር ውስጥ ምርታቸው 1 ትሪሊየን ዶላር ማጣታቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም መንግሥታት ክፍተቱን ለመሙላት ለአካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ትኩረት ሰጥተው ካልሰሩ እ.ኤ.አ በ2025 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ዶላር ሊያጡ ይችላሉ ሲሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል። የክህሎትና እውቀት ክፍተት፣ የኢንተርኔት ዋጋ አቅምን ያገናዘበ አለመሆን፣ ፆታዊ ትንኮሳ፣ የመጠቀሚያ መሳሪያዎች እጥረት የዘርፉ ፈተናዎች መሆናቸውን ዶክተር ካትሪን ገልጸዋል። በ2025 ኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታዋን የተሳካ ለማድረግ ስትራቴጂ ቀርፃ እየሰራች መሆኑን ጠቅሰው፤ ዕቅዱ የተሳካ እንዲሆን አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ፤ በኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፉ እየተወሰዱ ያሉ የለውጥ ሥራዎችና የተገኙ ውጤቶችን አብራርተዋል። በ2025 ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሁሉንም ባሳተፈ መልኩ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የሴቶችን የዲጂታል አቅም ለማሳደግ ክህሎትና እውቀት ላይ ትኩረት ያደረጉ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በሴቶችና በወንዶች መካከል ያለውን የዲጂታል ተጠቃሚነት ዕድልና ክህሎት ልዩነት ለማጥበብ እንደ አገር ጥናት እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል። በቀጣይም መሰል ተግባራት ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ጠቅሰው፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ እውን ይሆናል ብለዋል።
አካታች የዲጂታል ምጣኔ ሀብትን እውን ለማድረግ እውቀትና ክህሎትን ማሳደግ ላይ እየተሰራ ነው
Mar 27, 2023 110
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ አካታች የዲጂታል ምጣኔ ሀብትን እውን ለማድረግ እውቀትና ክህሎት ላይ ትኩረት አድርጋ እየሰራች መሆኑ ተገለጸ። አለም አቀፍ የሴቶች ቀን በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የሴቶችን የዲጂታል ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት በማድረግ ተከብሯል።   በዚሁ ጊዜ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ በኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፉ እየተወሰዱ ያሉ ሪፎርሞችን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ተግባራዊ እያደረገች ባለችው ዲጂታል 2025 መርሃ-ግብር ሴቶች ቴክኖሎጂን በሚፈለገው ደረጃ እንዳይጠቀሙ ካደረጉ ችግሮች ውስጥ የዲጂታል ክህሎትና እውቀት ማነስ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የሴቶችን የዲጂታል አቅም ለማሳደግ ክህሎትና እውቀት ላይ ትኩረት ያደረጉ ተግባራትን በማከናወን አካታች ምጣኔ ሀብትን ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም በሴቶችና በወንዶች መካከል የዲጂታል ዕውቀት ልዩነትን ለማጥበብ እንደ ሀገር ጥናት እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል። በቀጣይ በጥናቱ ግኝት መሰረት እስትራቴጂ በመቅረጽ ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ኢትዮጵያ በዲጂታል 2025 የያዘቻቸውን እቅዶች ለማሳካት ድጋፍ እንደሚያደርግ በመድረኩ ላይ የተገኙት የድርጅቱ ተወካይ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ አካታች ዲጅታል መርሃ ግብሮችን ባለመተግበር በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶች ከኢንተርኔት ተደራሽነት ውጭ እንደሆኑ በመድረኩ ተነግሯል።
የቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት ለኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚቀጥል ገለጸ
Mar 25, 2023 185
አዲስ አበባ መጋቢት 16/2015(ኢዜአ)፦ የቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት ለኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ እያደረገ ያለውን ድጋፍ እንደሚቀጥል አስታወቀ። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ፒ.ኤች.ዲ.) ከቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት ዋና ሊቀመንበር ሰር ቶኒ ብሌር ጋር በጽህፈት ቤታቸው ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለው ትብብርና በቀጣይ ለመስራት ባቀዷቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ማህበራዊ ትስስር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። የቶኒ ብሌር ኢንስቲትዩት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 (ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን) ስትራቴጂ ከዝግጅት ወቅት አንስቶ እስከ ማስፈጸም ሂደት በቴክኒክ(ባለሙያ)፣በኢ-ሰርቪስ ትግበራ ላይ ጥናት በማድረግ፣የማስፈጸም አቅም እንዲሁም የአደረጃጀትና የስራ ሂደትን ለማሻሻል የሚያስችል ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱ ተገልጿል። ኢንስቲትዩቱ ከዲጂታል መሰረተ ልማት አኳያ በዳታ ሴንተር፣በኢንተርኔት ተደራሽነት፣ በክላውድና በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ላይ በቀጣይ ሊያደርገው በሚችለው ድጋፍ ውይይት መደረጉ ተመላክቷል። በሌላ በኩል የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሄ ዘሚካኤል ለሰር ቶኒ ብሌር የዲጂታል መታወቂያን አገልግሎቶች አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ዳይሬክተሩ ኢንስቲትዩቱ ለአገልግሎቱ የሚያደርገውን ድጋፍ እና ከመሰረተ ልማት ጋር ያሉ ተግዳሮቶች ላይም ገለጻ አድርገዋል። የ69 ዓመቱ የእንግሊዝ የቀድሞ ፖለቲከኛ አገሪቷን ከእ.አ.አ 1997 እስከ 2007 በጠቅላይ ሚኒስትርነት አገልግለዋል።
ኢትዮ-ቴሌኮም በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የመሪነቱን ሚና እየተወጣ ነው-ፍሬህይወት ታምሩ
Mar 24, 2023 189
አዲስ አበባ መጋቢት 15/2015 (ኢዜአ) ኢትዮ- ቴሌኮም በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ውስጥ የመሪነቱን ሚና እየተወጣ መሆኑን የኢትዮ- ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ኢትዮ-ቴሌኮም በአዲስ መልክ ያበለጸገውን ቴሌ ብር "ሱፐር አፕ" የሞባይል መተግበሪያ ይፋ አድርጓል። መተግበሪያው ደንበኞች የዕለት ተዕለት ተግባራቸውን ለማቅለልና በቴክኖሎጂ የታገዘ የንግድ ስራዎችን ለማሳለጥ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። በአንድ ጊዜ ፈርጀ ብዙ የዲጂታል ግብይት አገልግሎቶችን እንዲያገኙና ለማንኛውም የግዢ ሂደት እንዲጠቀሙ የሚያስችል መተግበሪያ መሆኑም ተመላክቷል። ይህ አዲሱ መተግበሪያ አሁን በስራ ላይ ካለው የቴሌብር መተግበሪያ ጋር ተያይዞ የሚታዩ የአፈጻጸም፣ የሴኩሪቲ ሲስተም፣ የስልክ ዳታ የመያዝ አቅም ውስንነትንና ሌሎች የመሳሰሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል መሆኑም ተነግሯል። እንዲሁም የማይ- ኢትዮ- ቴል መተግበሪያንና ሌሎች መተግበሪያዎችን በአንድ በማካተት የተቀናጀ፣ ብቁ እንዲሁም አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘት የሚያስችል ነው ተብሏል። የኢትዮ -ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኩባንያው አገልግሎቱን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገ ይገኛል። የዲጂታል ኢኮኖሚን እውን የማድረግ ሥራን አጠናክሮ በመቀጠል ኢትዮ-ቴሌኮም በዘርፉ የመሪነት ሚናውን እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀም በቴክኖሎጂ መታገዝ ወሳኝ መሆኑን ተናግረው፤ በዛሬው ዕለት ይፋ የሆነውም መተግበሪያ ይህንኑ እንደሚያጎለብት ተናግረዋል። ሌላኛው የስማርት ስልክ አጠቃቀም መሆኑን ገልጸው አሁን ላይ በኔትወርክ ላይ ከተመዘገቡት 81ሚሊየን ቀፎዎች ውስጥ 46 በመቶ የሚሆኑት የስማርት ቀፎዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በዛሬው ዕለት ይፋ የተደረገው መተግበሪያ ቴሌ ብር ሱፐር አፕ ለተለያዩ አገልግሎት የምንጠቀምባቸው አፕሊኬሽኖችን በአንድ መተግበሪያ ላይ ሁሉንም መጠቀም የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ጊዜንና ወጭን በመቆጠብ ረገድ መተግበሪያው ትልቅ ሚና እንዳለውም ጠቁመዋል።        
ስፖርት
በደቡብ ኦሞ ዞን ባህላዊውን የዋና ስፖርትን ለማዘመን ጥረት እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ገለጸ
Mar 28, 2023 48
ጂንካ መጋቢት 19 / 2015 (ኢዜአ) በደቡብ ኦሞ ዞን የሚዘወተረውን ባህላዊ የውሃ ዋና ስፖርት በማዘመን በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚሆኑ ስፖርተኞችን ለማፍራት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ገለጸ። በኦሞ ተፋሰስ አካባቢ የሚገኙ አርብቶ አደሮች የዕለት ተዕለት መስተጋብር ውጤት የሆነው የውሃ ዋና ስፖርት በአካባቢው ከልጅነት እድሜ ጀምሮ ይዘወተራል። ስፖርቱን ለማበረታታት ያለመ የውሃ ዋና ስፖርት ውድድር በኦሞራቴ ከተማ አቅራቢያ በመምሪያው አዘጋጅነት ዛሬ ተካሂዷል። ይህን ባህላዊ የውሃ ዋና ስፖርት ላይ ዘመናዊ ዕውቀቶችን እና ክህሎቶችን መጨመርና ማከል ቢቻል ከአገር አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ በመሆን የአገሪቱን ስም የሚያስጠሩ ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍራት እንደሚቻል ተገልጿል። የደቡብ ኦሞ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ወሊ ኃይሌ እንደተናገሩት፤ በኦሞ ወንዝ ላይ በርካቶች እንደ ባህል አድርገው የዋና ስፖርትን ያዘወትራሉ። ከዚህ ልምድ ተነስቶ የዘወትር ተግባር እየሆነ የመጣው የውሃ ዋና ስፖርት ማሳደግ ቢቻል በዓለም አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪና ተወዳዳሪ ሊሆኑ የሚችሉ ተተኪ ስፖርተኞች ማፍራት የሚያስችል ዕድል መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ሁለት አመታት በዞኑ በውሃ ዋና ስፖርት ላይ በልዩ ትኩረት በተሰሩ ስራዎች ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸው፤ ከአገር ውስጥ አልፎ በውጭ አገራት ተወዳዳሪ የሆኑ ስፖርተኞችን ማፍራት እንደተቻለ ተናግረዋል። ይህን በማስፋት በተለይ በኦሞ ወንዝ ዳርቻ የሚገኙ ባህላዊ የውሃ ዋናተኞች ላይ በትኩረት ቢሰራ በርካታ ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍራት እንደሚቻል ገልፀዋል። ያለውን የውሃ ዋና ስፖርት እምቅ አቅም ለማሳደግ ውድድሮችን ማካሄድና ሁኔታዎች በማመቻቸት ትኩረት እንዲሰጠው እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ስፖርቱን ውጤታማ ለማድረግ የሁሉም ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል። በአሁኑ ሰአት ስፖርተኞቹ በወራጅ ወንዞች ላይ ልምምድ እያደረጉ በመሆናቸው ሳይንሳዊ የውሃ ዋና ቴክኒኮችን ለማስተማር ተግዳሮት እንደፈጠረባቸው ገልፀዋል። በመሆኑም ዘመናዊ የመዋኛ ገንዳ፣ የመዋኛ አልባሳት እና የመሳሰሉ ግብአቶችን በማሟላት ረገድ የክልሉና የፌዴራል የውሃ ዋና ፌዴሬሽኖች እገዛ እንዲያደርጉላቸው ጠይቀዋል። በመምሪያው የስፖርት ዘርፍ የስፖርት ውድድር እና ተሳትፎ ቡድን መሪ አቶ አስራት ጊዮርጊስ በበኩላቸው በኦሞ ተፋሰስ አካባቢ ያለውን የውሃ ዋና ስፖርት እምቅ አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ጠቁመዋል። ባህላዊው የውሃ ዋና ስፖርት ወደ ዘመናዊነት ማሳደግ ቢቻል በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚሆኑ ስፖርተኞችን ማፍራት እንደሚቻል ተናግረዋል ። የውሃ ዋና ስፖርት በጣም የሚወደው ስፖርት እንደሆነ የሚናገረው የኦሞራቴ ከተማ ነዋሪው ወጣት በለዋ ሎንጋርቾ፤ የዋና ስፖርት የሚያከናውኑበት የኦሞ ወንዝ የውሃ ዋና ቴክኒኮችን ለመለማመድ እንደማያስችላቸው ገልጿል። በቀጣይ መዋኛ ገንዳዎች ቢሰሩ፣ የተለያዩ ቴክኒኮችን የሚያስተምሩ አሰልጣኞች ቢሟሉና ሌሎች ድጋፎች ቢደረጉልን በስፖርቱ የተሻለ ውጤት ማምጣት እንችላለን ሲል ለኢዜአ ገልጿል። በአካባቢው የሚገኙ ስፖርተኞችን ለማበረታት በዳሰነች ወረዳ ኦሞራቴ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው በኦሞ ወንዝ ላይ የውሃ ዋና ስፖርታዊ ውድድር የተካሄደ ሲሆን በሁለቱም ፆታዎች አሸናፊ ለሆኑ ስፖርተኞች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።  
“በዛሬው ጨዋታ ጥሩ ውጤት ይዞ መውጣት የሚያስችል የስነ-ልቦና ዝግጅት አድርገናል”-አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
Mar 27, 2023 97
አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ)፦ በኮትዲቯር አስተናጋጅነት በሚካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ከጊኒ ጋር ሁለተኛውን የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ዛሬ ታደርጋለች። የሁለቱ አገራት ጨዋታ በሞሮኮ ራባት በሚገኘውና 45ሺህ ተመልካች በሚያስተናግደው ልዑል ሙላይ አብደላ ስታዲየም ከምሽቱ 4 ሰዓት ይካሄዳል። በምድብ አራት የሚገኙት ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም ባደረጉት ጨዋታ ጊኒ 2 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል። የዋልያዎቹ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የዛሬውን ጨዋታ አስመልክቶ በሰጠው አስተያያት “ከመጀመሪያው ጨዋታ በኋላ አብዛኛው ትኩረት የነበረው ተጫዋቾቹን ከሽንፈቱ በኋላ ከነበረው ስሜት ወጥተው ለዛሬው ጨዋታ በስነ ልቦናና አዕምሮ ዝግጁ እንዲሆኑ ማድረግ ነው” ሲል ገልጿል። በጊኒ ለተወሰደብን ብልጫ መልስ ለመስጠትና ጨዋታውን ለመቆጣጠር ከአዕምሮ ዝግጁነት ይልቅ አካላዊ ፍልሚያና ስሜታዊነት ላይ ትኩረት ማድረጋችን ለነሱ ይበልጥ እንዲመቻቸው ማድረጉን ተናግሯል። ይህም ተጫዋቾቹ ከጨዋታው ውጤት ለማግኘት ከነበራቸው ከፍተኛ ጉጉትና በአዕምሯቸው ስለው የገቡትና ሜዳ ላይ የነበረው ነባራዊ እውነት የተለያዩ ከመሆናቸው እንደሚመነጭ አመልክቷል። “በታዩት ክፍተቶች ላይ ውይይት መደረጉንና ከዛሬው ጨዋታ ጥሩ ውጤት ይዞ ለመውጣት ዝግጅታችንን ጨርሰናል” ነው ያለው አሰልጣኝ ውበቱ። የአማካይ ተጫዋቹ ጋቶች ፓኖም በሁለት ቢጫ ካርድ ምክንያት በቅጣት በዛሬው ጨዋታ የማይሰለፍ ሲሆን የተከላካይ መስመር ተጫዋቹ ምኞት ደበበ ከአንድ ጨዋታ ቅጣት መልስ ለዛሬው ጨዋታ ዝግጁ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የሁለቱን ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ የ36 ዓመቱ ቻዳዊ ኢንተርናሽናል ዳኛ አልሀጂ አላው ማህማት በዋና ዳኝነት ይመሩታል። ኢትዮጵያ በምትገኝበት ምድብ አራት ማላዊ ከግብጽ ነገ ከቀኑ 10 ሰዓት በቢንጉ ናሽናል ስታዲየም ይጫወታሉ። በምድብ አራት ግብጽ እና ጊኒ በተመሳሳይ ስድስት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበላልጠው አንደኛና ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል። ኢትዮጵያ በሶስት ነጥብ የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች። ዋልያዎቹ በአፍሪካ ዋንጫ የመሳተፍ እድላቸውን ለማስፋት የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ ይጠበቅባቸዋል።
ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድርን አትሌት መዲና ኢሳ በአንደኝነት አጠናቀቀች
Mar 26, 2023 141
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ የሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድርን አትሌት መዲና ኢሳ በአንደኝነት አጠናቀቀች።   አትሌት መዲና ኢሳ በመሪነት በማጠናቀቋ የ70ሺህ ብር ተሸላሚ ስትሆን በተጨማሪም በውድድሩ አዲስ ክብረ-ወሰን በማስመዝገቧ የ50ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶላታል። በውድድሩ አትሌት ፅጌ ገብረ ሰላማ 2ኛ እንዲሁም አትሌት መልክናት ውዱ 3ኛ ደረጃን ይዘው በማጠናቀቃቸው እንደቅደም ተከተላቸው የ45ሺህ ብር እና የ30ሺህ ብር ተሸላሚ ሆነዋል። በውድድሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረ ሥላሴ፣ አትሌት መሰረት ደፋር፣ አትሌት ለተሰንበት ግደይን ጨምሮ የተለያዩ አትሌቶችና እንግዶች ተገኝተዋል። የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎሜትር ሩጫ ”ቦታዬ፤ መብቴ፤ ድምፄ” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው በዚህ ውድድር አትሌቶች፣ 15 ሺህ የጤና ሯጮች፤ እንዲሁም አምባሳደሮች እየተሳተፉ ነው።
20ኛው የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር እየተካሄደ ነው
Mar 26, 2023 135
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሚዘጋጀው 20ኛው የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር እየተካሄደ ነው። ውድድሩ መነሻና መድረሻውን አዲስ አበባ ቦሌ አትላስ አካባቢ አድርጎ እየተካሄደ ነው።   የዘንድሮው ዓመት ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ”ቦታዬ፤ መብቴ፤ ድምፄ” በሚል መሪ ቃል ነው የሚካሄደው። በዚህ ውድድር ላይ በአትሌቶች፣ የጤና ሯጮች፣ እንዲሁም አምባሳደሮች ይሳተፋበታል።   በውድድሩ በሴት አትሌቶች መካከል በሚደረገው ፉክክር በአንደኝነት ለምታጠናቅቀው አትሌት የ70ሺህ ብር ሽልማት መዘጋጀቱም ታውቋል። እንዲሁም ውድድርን ሁለተኛ ሆና ለምታጠናቅቅ 45ሺህ ብር፤ 3ኛ ሆና ለምታጠናቅቅ ደግሞ የ30ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት መዘጋጀቱም ተጠቁሟል።   ክብረ-ወሰን የሚያሻሽሉ አትሌቶች ተጨማሪ የገንዘብ ሽልማት የሚያገኙ ይሆናል። በውድድሩ በአትሌቶች መካከል ከሚደረገው ውድድር በተጨማሪ 15ሺህ የጤና ሯጮች እየተሳተፉ ነው።   በሩጫ ውድድሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ፣ አትሌት መሰረት ደፋር እና አትሌት ለተሰንበት ግደይ ተገኝተዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በምሥራቅ ባሌ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን መቀነስ ታሳቢ ያደረገ 155ሺህ ሄክታር መሬትን የሸፈነ የተፋሰስ ልማት ስራ መሰራቱ ተገለጸ
Mar 26, 2023 111
መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ) በምሥራቅ ባሌ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን መቀነስ ታሳቢ ያደረገ 155 ሺህ ሄክታር መሬትን የሸፈነ የተፋሰስ ልማት ስራ መሰራቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። በዞኑ ባለፉት ሁለት ወራት ሲካሄድ የነበረው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ መጠናቀቁን ጽህፈት ቤቱ አስታውቋል። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት እንደገለጸው ባለፉት ሁለት ወራት በተከናወነው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራ 155ሺህ ሄክታር መሬት የሸፈነ የተፋሰስ ልማት ስራ ተከናውኗል። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ይሳቅ በተቀናጀ የአፈርና ውኃ ጥበቃ የተከናወኑ ሥራዎች የድርቅ ተጋላጭነትን በመቀነስ በኩል ጉልህ አስታዋጽኦ እያበረከቱ ነው። በዞኑ ስምንት ወረዳዎች ከ155ሺህ ሄክታር መሬትን በመሸፈን በተከናወነው በዚህ ሥራ 3ሺህ ሄክታር መሬትን ከእንስሳት ንክኪ ማካለልን ጨምሮ የችግኝ ዝግጅት፣ 20ሺህ ኪሎ ሜትር የማሳና የተራራ ላይ እርከን ስራ፣ የግጦሽ መሬት ልማትና ሌሎች የድርቅ ተጋላጭነትን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ከድር እንዳሉት፣ በዞኑ በተደጋጋሚ እየተሰሩ የሚገኙ የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎች የድርቅ ተጋላጭነትን ከመቀነስ በተጓዳኝ የሥራ ዕድል ምንጭ እንዲሆኑ ከ4ሺህ የሚበልጡ ወጣቶችን በዘርፉ ማደራጀት ተጀምሯል። በዞኑ የዳዌ ቃቸን ወረዳ የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ አሚን እንዳሉት፣ በአካባቢያቸው በተደጋጋሚ እያጋጠመ የሚገኘውን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ ለተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ትኩረት ተሰጥቷል። በወረዳው የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ የተከናወነባቸው ተፋሰሶች በዘላቂነት እንዲጠበቁ ከ30 የሚበልጡ ወጣቶችን በተፈጥሮ ኃብት ማህበራት እንዲደራጁ ተደርጓል ብለዋል። ወጣቶቹ ከእንስሳት ንክኪ በተከለሉና በተፈጥሮ ኃብት በተሸፈኑ አካባቢዎች ውስጥ የንብ ማነብ፣ የእንስሳት መኖ ልማት፣ ሌሎች የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን እንደሚያከናውኑ ነው የገለጹት። በዳዌ ቃቸን ወረዳ በአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ከተሳተፉ ነዋሪዎች መካከል አቶ ያህያ አብዱልወሃብ በሰጡት አስተያየት፣ የተቀናጀ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ሥራዎች የድርቅ ተጋላጭነትን እንደሚቀንሱ በማመን በስራው መሳተፋቸውን ተናግረዋል። በተለይ ዘንድሮ በአካባቢያቸው በተከናወኑ ሥራዎች ላይ ወጣቶች እንዲደራጁ መደረጉ ሥራውን ውጤታማ ያደርገዋል ነው ያሉት። ወጣት ሙክታር መሐመድ በበኩሉ፣ በሰው ሰራሽ ተጽእኖ የተነሳ አካባቢያቸው ተራቁቶ እንደልብ ይፈሱ የነበሩ ወንዞች በመድረቃቸው ለድርቅ መጋለጣቸውን አስታውሰዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎች የተራቆተው አካባቢ አረንጓዴ እየለበሰ መምጣቱ ተስፋ እየሰጣቸው መሆኑን ነው የገለጹት። በአሁኑ ወቅት ከሌሎች 15 የአካባቢያቸው ወጣቶች ጋር የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ማህበራት በመደራጀት በንብ ማነብና የእንስሳት መኖ እየተሳተፈ መሆኑን አመልክቷል።  
በአማራ ክልል በዘንድሮው የበጋ ወራት በ331 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራ ተከናውኗል - የክልሉ ግብርና ቢሮ
Mar 24, 2023 211
ሰቆጣ መጋቢት 15 ቀን 2015(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በዘንድሮው የበጋ ወራት በ331 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራ መከናወኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ በበጋው ወቅት የተከናወኑ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎችን እንዲጠብቁ ለአርሶ አደሮች በባለቤትነት የማስረከብ መርሐግብር በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ደሃና ወረዳ ሽመላ ቀበሌ ጋውሳ ተፋሰስ ዛሬ ተካሂዷል።   የአማራ ክልል የግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር አልማዝ ጊዜው የክልሉን የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ውጤታማ ለማድረግ ከ14 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የዞንና ቀበሌ ባለሙያዎች የክህሎት ስልጠና መሰጠቱንና 34 ሺህ የሚደርሱ የስራ መሳሪያዎች ለዞኖች መከፋፈላቸውን ለኢዜአ ገልጸዋል። በክልሉ 8 ሺህ 548 ተፋሰሶች ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራዎች ለማከናወን ታቅዶ፤ በ8 ሺህ 596 ተፋሰሶች ላይ ስራዎቹ መካሄዳቸውን አመልክተዋል። በልማቱ በ331 ሺህ ሄክታር ላይ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች መከናወናቸውንና በስራዎቹ ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ጠቁመዋል። የተፈጥሮ ሃብት ልማት በዘላቂነት በማከናወን የዜጎችን ሕይወት ለመቀየር የሚያስችሉ ተግባራት ለማከናወን መታሰቡን ነው ዶክተር አልማዝ ያስረዱት። በቀጣይም የለሙ ተፋሰሶችን በስነ ሕይወታዊ ዘዴዎች የመሸፈንና የኢኮኖሚ ምንጭ የሚሆኑትን የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ እንዳሉት፤ በአስተዳደሩ በ277 ተፋሰሶች ውስጥ የሚገኝ 4 ሺህ 927 ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ተካሄዷል።   በልማቱም ከ82 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውንና በዞኑ ባለፉት ዓመታት የተካሄዱት ተፋሰሶች የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እንዳሳደጉትም ገልጸዋል። በተለይም በተራራ ላይ የተሰሩ የጠረጴዛ እርከኖች ለበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንና ስራዎቹን በቀጣይም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ደሃና ወረዳ የሚገኙ አርሶ አደሮች በአካባቢያቸው ባለፉት ዓመታት በወረዳው በተካሄዱት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች በመሳተፍ የእርሻ መሬታቸውን ለም አፈር በማሳ ውስጥ በማስቀረት ምርታማነታቸውን ማሳደግ መቻላቸውን ገልጸዋል።   ዘንድሮ የተካሄዱት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራዎች በአግባቡ እንዲጠበቁና እንዲያገግሙ በየአካባቢያቸው የተፈጥሮ ሃብት ኮሚቴ ተዋቅሮ ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። በአማራ ክልል በዘንድሮው ዓመት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ሶስት ቢሊዮን ብር የሚገመት የጉልበት አስተዋጽኦ መደረጉን የክልሉ ግብርና ቢሮ መረጃ ያመለክታል'።  
በአማራ ክልል የ2015 የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ የሽግግርና ርክክብ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 24, 2023 162
ሰቆጣ መጋቢት 15/2015(ኢዜአ) የአማራ ክልል የ2015 የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ የሽግግርና ርክክብ መርሃ ግብር በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ደሃና ወረዳ እየተካሄደ ነው። በወረዳው እየተካሄደ ባለው መርሃ ግብር የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኃይለማርያም ከፍያለውን ጨምሮ የክልልና የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።   በክልሉ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራው ከጥር 17 ቀን 2015 ጀምሮ ሲካሄድ ቆይቷል። ሽግግርና ርክክቡም በህዝብ ንቅናቄ የለማውን ተፋሰስ በየአቅራቢያው ለሚገኙ ነዋሪዎች በማስረከብ በስነ ህይወታዊ ዘዴ በዘላቂነት እንዲለማ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል። "ይህም ተፋሰሱን በመጠበቅና በማልማት በቋሚ አትክልትና ፍራፍሬ፣ በንብ ማነብና መሰል የሥራ ዘርፎች ተደራጅተው ለሚገቡ ወጣቶች የኢኮኖሚ ምንጭ ለመሆንም ያስችላል" ብለዋል። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ በዞኑ ስድስት ወረዳዎች በ119 ቀበሌዎች በህዝብ ተሳትፎ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራዎች መካሄዳቸውን ተናግረዋል። በዚህም በ 2 ሺህ 775 ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ የተሰራ ሲሆን፣ በ2 ሺህ 152 ሄክታር መሬት ላይ ደግሞ ነባር የለሙ ተፋሰሶች ጥገና መደረጉን አስታውቀዋል። በልማት ሥራው ከ82 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን የገለጹት ኃላፊው፣ በሥራዎቹ ከ147 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የጉልበት አስተዋጽኦ ማበርከት ተችሏል ብለዋል።  
የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎችን ጥራትና ተደራሽነት ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል - የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
Mar 23, 2023 182
አዲስ አበባ መጋቢት 14/2015(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የትንበያና የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃዎችን ጥራትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የዓለም የሚቲዎሮሎጂ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ62ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደረጃም ለ42ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተከብሯል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ክንፈ ሃይለማርያም በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎችን ለማኅበረሰቡ ተዳራሽ በማድረግ ደኅንነት ለማስጠበቅና ልማትን ለማፋጠን እየተሰራ ነው። ትክክለኛ የአየር ትንበያ መረጃዎች ለጥናት ምርምር ጭምር እንደሚያግዙ ጠቁመው ትክክለኛ የአየር ትንበያ መረጃ እንዲኖር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ጎርፍና ድርቅ ያሉ ክስተቶች በአገሪቷ እየተበራከቱ መሆናቸውን አንስተው እነዚህን ለመቋቋምም የተጠናከረ የአየር ሁኔታ መከታተያ፣ መተንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት በመገንባትና በመዘመን ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለዚህም በሰው ሃብትና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ራሱን በማሻሻል ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል። በዓለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ ቢሮ ዳይሬክተር ዶክተር አግነስ ኪጃዚ በበኩላቸው የሚቲዎሮሎጂ ትንበያ መረጃ በተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመታገዝ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች የግብርና ሥራዎች ወቅታቸውን ጠብቀው እንዲከናወኑ ከማድረጉም ባለፈ ምርቶች በጊዜ ተሰብስበው ለተፈለገላቸው ዓላማ እንዲውሉ ከማገዝ አንጻር ሰፊ ጠቀሜታ አላቸው።    
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 562
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተገለጸ
Dec 20, 2022 564
አዲስ አበባ ታኅሳስ 11/2015 (ኢዜአ) አህጉራዊው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና አፍሪካ ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ግንኙነትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተመላከተ። የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ከአፍሪካ ጋር ያላት የንግድ ትስስር ከባህረ-ሰላጤው ሃገራት መካከል በቀዳሚነት እንደሚጠቀስም ተገልጿል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዊሊያም ስቴንሀውስ ከሲ ጂ ቲ ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በተለይም ዱባይ የአፍሪካን ንግድና ኢንቨስትመንት በተመለከተ ዋና ማዕከል ሆናለች ብለዋል። በዱባይ 25ሺህ ገደማ የአፍሪካ ካምፓኒዎች እንደሚንቀሳቀሱ አመልክተው ይህም ሀገሪቱ በነጻ የንግድ ቀጣናው የቢዝነስ አጋር እንድትሆን አስችሏታል ነው ያሉት። አፍሪካውያን ባለሃብቶች የግብይት ማዕከላቸውን በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በማድረግና ምርቶችን ወደ አህጉሪቷ በማስገባት በነጻ ንግድ ቀጣናው ስር የገልፍ ሀገራትን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደጉት እንደሚገኝም አስገንዝበዋል። የዱባይ ወደብ በአፍሪካ ያለው ተደራሽነት መስፋፋትም አፍሪካ ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ጋር የሚኖራትን የሎጀስቲክስ አቅርቦት እንደሚያሳድግ በመረጃው ተመላክቷል። ከገልፍ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት ከኢኮኖሚያዊ ትስስር ባለፈ ዲፕሎማሲያዊና ወንድማማችነትን መሠረት ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤሜሬት የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ ናቸው። አምባሳደሩ እንደሚሉት ከመካከለኛው ምስራቅ መነሻቸውን ያደረጉ ባለሃብቶችና የቢዝነስ ሰዎች ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጋር በልዩ ልዩ ዘርፎች ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ይገኛል። እ.አ.አ በጥር 2021 ተግባራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ከአጀንዳ 2063 ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የአህጉሪቱን ወሳኝ የኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም የዲጂታል ንግድ፣ የኢንቨስትመንት ትስስርና ሌሎች የንግድ ግንኙነቶችን በነጻ የንግድ ቀጣና ለማከናውን የተካሄደ ስምምነት ነው።
ሐተታዎች
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 61
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
ውጣ ውረድ የማይበግረው አጋርነት
Mar 17, 2023 314
በሰለሞን ተሰራ ኢትዮጵያ በሥልጣኔ ቀደምትና ታሪካዊት ሀገር ነች። ቅሉ ከውጭ ሀገራት ያላትን ዘመናዊው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቅኝት የጀመረችው በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑ በታሪክ ይጠቀሳል። በተለይም ኢጣሊያ በአውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ1896 በአድዋ እንዲሁም በድጋሚ በ1935 ያደረገችው የግፍ ወረራ ኢትዮጵያ የዓለምን ፖለቲካ በቅጡ አሰላለፍ ተረድታ አጋር ሀገራትን እንድትሻ ዐይኗን ገልጦላታል። በዚህም ድኅረ-አድዋ ድል በርካታ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መስርተዋል። የወቅቱ ልዕለ-ኃያል ሀገር አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷ የተመሰረተውም በዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና በፕሬዝዳንት ሩዝቬልት መንግሥት ተወካይ ሮበርት ስኪነር መካከል በፈረንጆቹ አቆጣጠር 1903 በተደረሰው የንግድ አጋርነት ስምምነት ነበር። ድኅረ-ስምምነቱም በፈረንጆቹ በ1909 የአሜሪካ ሌጋሲዮን በአዲስ አበባ የተመሰረተ ሲሆን ሆፍማን ፊሊፕ የተባሉት ቋሚ መልዕክተኛ የአሜሪካ ቆንስላ ተሿሚ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአፄ ምኒልክ አቅርበዋል፡፡ ከ120 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የኢትዮ-አሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በጽኑ ወዳጅነትና የጋራ ጥቅሞች ላይ የተመሰረተ እንደነበር ይወሳል፡፡ ሀገራቱ ጥቅማቸውን በጠበቀ መልኩ የመሰረቱት ግንኙነት ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማምጣት ታሳቢ ያደረገ መሆኑም አይዘነጋም፡፡ የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራን ተከትሎ ቆንስላዋን የዘጋችው አሜሪካ፤ ኢትዮጵያ በአርበኞቿ ትግል ነፃነቷን ስታረጋግጥ በፈረንጆቹ አቆጣጠር በነኅሴ 1943 በድጋሚ ቆንስላዋን በመክፈት ግንኙነቷን አስቀጥላለች። በተመሳሳይ ወቅት ኢትዮጵያ በአሜሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የቆንስላ ቢሮ ከፍታ ዕውቁን ዲፕሎማት ብላታ ኤፍሬም ተወልደመድኅንን በቋሚ መልዕክተኛነት ሾማለች። በአውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ1952 የተደረገው 'ፖይንት ፎር' የተሰኘው የተቋማት ቴክኒክ ድጋፍ ስምምነት ለሁለቱ ወዳጅ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ይበልጥ መሰረት የጣለ እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ በዚህ ስምምነትም የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የአውራ ጎዳና ባለሥልጣን እና የኢትዮጵያ ካርታ ሥራ ድርጅት በአሜሪካ መንግሥት ድጋፍ ተቋቁመዋል። የሁለትዮሽ ግንኙነቱ አድማሱን እያሰፋ፣ ሥር እየሰደደ ቀጥሎ ኢትዮጵያ ጦር ሠራዊቷን እንድታጠናክር በአነስተኛ የጦር መሳሪያዎች፣ ተሽከርካሪዎችና ወታደራዊ ሥልጠናዎች ተጨባጭ አጋርነት አሳይታለች። የደርግ ወታደራዊ መንግሥት ሥልጣን በተቆጣጠረ ማግስት ግን በዘመኑ በነበረው ዓለም አቀፋዊ ርዕዮተ- ዓለም ልዩነት ሳቢያ የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሻክሮ ሌላ መልክ ያዘ። በተለይም የደርግ ሊቀ-መንበር የነበሩት ሌተናል ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ወደ ሶቪየት ሕብረት አቅንተው የጦር መሳሪያ ድጋፍ መፈራረማቸው አለመግባባቱን ይበልጥ አባባሰው። በዚህም አሜሪካ በኤርትራ የነበረውን የቃኘው ሻለቃ ጣቢያዋን ዘግታ ወጣች። ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ከአምባሳደር ደረጃ በማውረድ በጉዳይ አስፈጻሚ ሲገናኙ ቆይተዋል፡፡ ኢሕአዴግ ወደ ሥልጣን ሲመጣ የሀገራቱ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ቀድሞ ወደነበረበት የአምባሳደር ደረጃ በመመለስ ከአሜሪካ ጋር የነበረው ግንኙነት መልሶ እንዲያንሰራራ አድርጎታል፡፡ ባለፉት 30 ዓመታት አሜሪካ በጤና፣ በሰብዓዊ ድጋፍ፣ በመልካም አስተዳደርና በዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ላይ በምታደረገው ድጋፍ በመታገዝ በጋራ ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ ከሦስት ዓመታት ወዲህ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ አሜሪካ መርህን ያልተከተለ አካሄድ በሀገራቱ መካከል የነበረውን ወዳጅነትና አጋርነት ላይ ጥቁር ጥላ ማጥላቱ አይዘነጋም፡፡ ነገር ግን ባለፉት ሦስት ዓመታት በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ሻክሮ የቆየውን ግንኙነት በማደስ የነበረውን ጠንካራ ወዳጅነት በድጋሚ የሚያጸኑ ጅማሮዎች ተስተውለዋል። በተለይም ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በአፍሪካ ሕብረት መሪነት የተደረሰውን የሰላም ሰምምነት ተከትሎ የሀገራቱ መቃቃር እየረገበ ሲሆን የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ኢትዮጵያን በተደጋጋሚ እየጎበኙ ነው፡፡ ይህን ተከትሎ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ከትናንት በስቲያ አዲስ አበባ የገቡት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፤ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ተነጋግረዋል። አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ያደረጉት ውይይት ዘርፈ-ብዙ አጋርነትን ለማጠናከር መግባባት የተደረሰበት እንደነበርም በሁለቱም ወገኖች ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ውይይቱ በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደሆነና በኢትዮጵያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ስምምነት የተደረሰበት እንደሆነ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በሰላም ስምምነቱ ላይ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ተቀባይነት ማግኘቱንም ጠቅሰዋል። በኢኮኖሚው መስክ በተለይም በግብርና እና በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ባተኮሩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት መነጋገራቸውን በመልዕክታቸው ጠቁመዋል። በተመሳሳይ አንቶኒ ብሊንከን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ባደረጉት በሁለትዮሽና በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በትኩረት መክረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ሚኒስትሮቹ ለረዥም ዘመን የዘለቀውን የኢትዮ-አሜሪካ ትብብር እና አጋርነት ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ተነጋግረዋል። በኢትዮጵያ አዲስ የመረጋጋትና የሰላም ምዕራፍ መከፈቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን አብራርተውላቸዋል። የሰላም ምዕራፍ የበለጠ እንዲጠናከርና የሰመረ እንዲሆን ከዚህ ባለፈም የሀገሪቱን በጎ ገጽታ እንዲላበስ መንግሥት በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ እምርታ እንዲመጣ ለሰላም ስምምነቱ ተፈፃሚነት መንግሥት አሁንም ቁርጠኛና ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ጠቅሰው፤ በመልሶ ግንባታ እና መልሶ ማቋቋም ተግባር የአሜሪካ መንግሥት እንዲደግፍም ጠይቀዋል፡፡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በበኩላቸው፤ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሻገር አሜሪካ በትብብር መንፈስ እንደምትሰራ እና አሜሪካ ሁለንተናዊ ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። አሜሪካ ለድርቅ ተጎጂዎች እና ለስደተኞች የምታደርገው ድጋፍ አለመቋረጡ የሁለቱ ሀገራት አብሮነት ተጠናክሮ መቀጠሉን ይጠቁማል፡፡ የብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝት ከኢትዮጵያ መጀመሩም ዛሬም ኢትዮጵያ በአሜሪካ መንግሥት ዐይን ያላትን ቀዳሚ ሥፍራ ያመለክታል። አንቶኒ ብሊንከን የሰላም ትግበራ ሂደቱ በመልካም ሁኔታ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ የበለጠ እንዲጠናከር የአሜሪካ መንግሥት ሁለገብ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የሁለቱን ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆኑን ማረጋገጡን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ እያደረገች ያለውን ጥረት አሜሪካ በአድናቆት እንደምትመለከተውና የሚበረታታ መሆኑን ብሊንከን ገልጸዋል። የብሊንከንን ጉብኝት ተከትሎ አሜሪካ 331 ሚሊየን ዶላር ተጨማሪ የሰብዓዊ ድጋፍ ለኢትዮጵያ እንደምታደርግ አረጋግጣለች። ድጋፉም በተለያዩ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ ወገኖች ነፍስ አድን ሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።  
የሴቶች ቀን ሲታሰብ
Mar 8, 2023 501
የሴቶች ቀን ሲታሰብ የሰው ልጅ ሕይወትን ቀላል ባደረጉ የፈጠራ ስራዎቻቸው የምናስባቸው እንስቶች በቀዳሚነት ይነሳሉ። በተለያዩ መስኮች አሻራቸውን ያሳረፉ እንስቶች ቁጥራቸው ከፍተኛ ቢሆንም በዚህ ጽሑፋችን ግን በኬሚስትሪና ፊዚክስ ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ ባበረከቱት አስተዋጽኦ በኖቤል ሽልማት እውቅና የተሰጣቸውን የየዘመኑ ፈርጦች እንዳስሳለን። ከነዚህ ፈርጦች መካከል በኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤልን ሽልማትን ከሴቶች ቀዳሚ በመሆን በቀዳሚነት ያሸነፉት ሜሪ ኩሪ ይወሳሉ። ይልቁንም እ.አ.አ በ1903 በኬሚስትሪ ዘርፍ የተቀበሉትን የኖቤል ሽልማት በድጋሚ በ1911 በመሸለም ብቸኛነት ስማቸው ይነሳል። በ1967 በፖላንድ ዋርሶ የተወለዱት ማሪ ኩሪ ለዘመናዊው የሳይንስና ኬሚስትሪ ዘርፍ ውለታን ከዋሉ ስመጥር ተመራማሪዎችና በጨረራ ህክምና ፈጠራ የዘርፉ ፈር ቀዳጅ በመሆን የአለምን የራዲዮአክቲቪቲ እይታን የቀየሩ ጀግና ናቸው።   የሜካኒካልና ኤሮስፔስ ተመራማሪዋ ፍራንሲስ አርኖልድ ደግሞ በህክምናናና በታዳሽ ኃይል ዘርፍ አሻረቸውን በጉልህ ካኖሩ ተመራማሪዎች መካከል ይጠቀሳሉ። አሜሪካዊቷ ፍራንሲስ ለታዳሽ ኃይል እና ለፋርማሲ አገልግሎት የሚውል አዲስ ኢንዛይም በምርምር በማግኘት በዘረፉ አሻራቸውን አኑረዋል። ለዚህም አስተዋጽኦዋ እ.አ.አ በ2018 በኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤልን ሽልማት አሸንፈዋል። የኤድስን ስርጭትን በመከላከል ረገድ ሰፊ አበርክቶ ያላቸው የህክምና ተመራማሪዋ ፍራንሶዝ ባሪሲኖሲም የሴቶች ቀን ሲታሰብ ከሚወሱ አንስቶች አንደኛዋ ናቸው። ባሪሲኖሲ የኤች አይቪ ኤድስን ከገዳይ በሽታነት መታከምና መቆጣጠር ወደ ሚችል በሽታነት ለመቀየር የኤች አይቪ ኤድስ ምርመራን በማላቅ ረገድ ሚናቸው የጎላ እንደሆነ ይወሳል። በ1947 በፓሪስ ከተማ የተወለዱት ባሪሲኖሲ “ሳይንስን ለሰው ልጆች ጥቅም እንዲውል እንሰራለን” በሚለው አባባላቸው ይታወቃሉ። ኤድስን በመከላከል ላደረጉት አስተዋጽኦም በፊዚዮሎጂ/ሕክምና ዘርፍ እ.አ.አ በ2008 የኖቤል ሽልማትን አግኝተዋል። ያለ ህክምና ትምህርት የሚሊዮኖችን ሕይወት በታደገው የወባ በሽታ መከላከያ ፈጠራቸው አለም እውቅና የተሰጣቸው ቱ ዩዩ በሴቶች ቀን የምናመሰግናቸው ሌላኛዋ ተመራማሪ ናቸው። ቻይናዊቷ ቱ ዩዩ ባህላዊውን የወባ በሽታ መከለከያ ህክምና ወደ ዘመናዊ በመቀየርና በማስተዋወቅ ነው ስመ ገናና የሆኑት።   የወባ በሽታን በመከላከል ረገድ በአለም አቀፍ ደረጃ ጉዙፍ አሻራቸውን ላስቀመጡት ተመራማሪ ባለውለታነት እ.አ.አ በ2015 በፊዚዎሎጂ/ ህክምና ዘርፍ ሳይንስ ምድብ የመጀመሪያዋ ቻይናዊት በመሆን የኖቤል ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የሰው ልጆችን ሕይወት ካቀለሉ አለም አቀፍ ፈጠራዎች መካከል የተጠቀሱትን ጨምሮ በሌሎችም ዘርፎች የሴቶች ተሳትፎ የጎላ መሆኑ ይታወቃል።
ሴትነት እና እናትነት
Mar 8, 2023 743
(አየለ ያረጋል) እስኪ መላ ስጪኝ መላ ካንቺ ይገኛል እኔማ ወንድ ነኝ ይደናገረኛል… (የማኅበረሰቡ ቃላዊ ግጥም) ሴትነት እናትነትን ለመግለጽ ቀርቶ በጥቂቱ ለመረዳት የ’እናት ልብ’ መታደል የሚሻ ይመስላል። ጥቂት ወንዶች ይህን ጸጋ ይቸራሉ። ልክ እንደ ዶክተር ይሁኔ አየለ። የስነ-ምግብ ሳይንቲስቱ ዶክተር ይሁኔ አየለ ‘እናት’ በሚል ርዕስ ባሳተሙት ድንቅ መጽሐፍ የሴትነት እና እናትነትን ከፍታ በ’ኩርሽም’ ቃላት ተራቀውበታል። የሴቶች ቀንን (ማርች-8) ሰበብ በማድረግ ይህን ጽሑፍ ሳዘጋጅ መታሰቢያነቱ እናትን አስበው በ‘እናትነት’ ቅን ልቦና ‘እናትን’ ላበረከቱልን ዶክተር ይሁኔ አየለ ነው። ‘እናት፤ የሴት ልጅ ስንክሳር፤ ከቤተሰባዊ ሕይወት እስከ ሐልዮመንበርት’ በሚል ርዕስ በቅርቡ ባሳተሙት (በ406 ገፆች በተቀነበበ) አርበ ጠባብ መጽሐፍ ሴትነትን ከዘፍጥረት እስከ አሁን ዘመናትን ዋጅተው፣ እናትነትን ከሴትነት ዘንቀው፣ የእናትነት ጸጋን ከነባራዊ ሃቅ ጋር አሰነናስለው፣ የእናትነትን ልዕለ-ተፈጥሮ አርቅቀው፣ የዓለምን ክብር-ነሽነት ከነገረ-ሃይማኖት እስከ ነገረ-ባህልና ፍልስፍና ፈትተው፣ የማኅበረሰቡን ምልከታ ዝንፈት እና ሚዛን ጉድለት ከማኅበራዊ እስከ ፖለቲካዊ መገለጫዎች አዛምደው አቅርበውታል። ዶክተር ይሁኔ አየለ “እናት” በተሰኘ እናት የሆነ መጽሐፋቸው እናትነትን በልኩ ነጽረውታል። ሴትነት በኢትዮጵያ የአስተሳሰብ ሰለባነቱን፣ ነገረ-ሴትነትን ከንጽረተ-ሴትነት ቃኝተውታል። በእሳቤ ሚዛን ሰለባነት ዓለም ውስጥ ከንግስት ማክዳ እስከ ንግስት ፉራ፣ ከሰብለ ወንጌል እስከ ድል ወንበራ፣ … ብርቱ ኢትዮጵያዊት ሴቶችን ሕይወት ጨልፈውታል። የሴትነትን ጸጋዎች ጨልፈው በሴትነት ላይ የሚፈጸሙ የሀበሻ ግፎችን ተንትነውበታል። ሴቶች የማኅበረሰቡ ግፍ ሰለባዎች፣ የማኅበራዊ ፍትህ ጉድለት ሰለባዎች እንደሆኑ በቅጡ ገልጸውታል። ዳሩ ሴትነት ጀግና እና ብልህ፣ የቤተሰብ መሰረት፣ የደስታና እልልታ እናት፣ ቃል ኪዳንና ክብር ጠባቂ እንደሆነ ገልጸዋል። “ሴት ልጅ ባለብዙ ጸጋዎች ናት። ከጸጋዎቿ መካከል ጀግንነት እና ብልሃት ይጠቀሳሉ። … ሴት ልጅ ባህልን ፈጥራ የማኅበራዊነትን ማስተሳሰሪያ ገመዶች ገምዳ አስተሳስራ ማኅበረሰብን የተከለች ሥርዓት ናት። … ቤተሰብ የአንድ ማኅበረሰብ የመጀመሪያ ተቋም ነው። የተቋሙ ባለሥልጣን (እመቤት) ሴት ናት። ያቺ ሴት እናት ናት። ቤተሰብ የስብዕና መሰረት የሚባለው እናትን ምሰሶ አድርጎ ነው” (ገጽ-285) ሴት ልጅ መለኛ መሆኗን ማኅበረሰባችን ቢያምንም ሴትነትን ግን እንዳላከበረ አሉታዊ ይትባህልና ኪነተ- ቃሉን ዘይቤ ያወሳሉ። በእርግጥ የእናትን ምቹነት እና ዋጋ ከፋይነት የሚያትቱ የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎችም አሉ። ለምሳሌ ዳንኤል አበራ “የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎች” በሚለው መጽሐፋቸው “እናት ትረገጣለች እንደመሬት፤ እናት ለልጄ ልጅ ለነገዬ፤ እናቷን አይተህ ልጅቷን አግባ፤ እናት የሌለው ልጅ እንደ ጌሾ፤ ሳይበላ የበላ ሳይናገር ዋሾ…” የሚሉ ምሳሌያዊ ንግግሮችን አስፍረዋል። መላኩ ይርዳው የተባሉ ጸሐፊ ‘ደቦ ቅጽ-፩’ ከተሰኘው የ60 ደራሲያን ሥራዎችን ያካተተ መጽሐፍ ውስጥ ‘የሴትነት ጸጋ’ በሚል በጻፉት መጣጥፍ ሴትነትን ከፍቅር፣ ከጥበብ፣ ከብልሃትና ልዕልና ጋር አቆራኝተውታል። “ሴት ልጅ ቅኔ ናት፤ ከተባለላት፣ ከተጻፈላት፣ ከተዜመላት በላይ የረቀቀች ረቂቅ ቅኔ ናት። እስከዛሬ ከያኒያን ስለሴት ከተራቀቁት፣ ከተጠበቡት ሁሉ እኔ ለማውቃት ሴት ሁሉ የሚመጥኑ ሆነው አልታዩኝም። የሴትነት ጸጋው ብዙ ነውና የሴትን ትክክለኛ ማንነት መርምረን አጥንተን የደረስንበት ውስጠ-ስሪቷን አጥንተን የተረዳነው አይመስለኝም።… ከታላቅነቷ፣ ከብልሃቷ፣ ከረቂቅነቷ፣ ከመግዛት አቅሟ፣ ከርህራሄዋ፣ ከሰላማዊነቷ ከሌሎችም አያሌ በረከቶች አንጻር ለሴት ልጅ የተደረገላት፣ የተነገረላትና የሆነላት ሁሉ ያንስብኛል” ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) ስለሴት ልጅ ጭቆና የታገለ እና ስለክብሯ የዘመረ ምሁር ነው። ስለሴት ልጅ ስቃይና ሰቆቃ አትቷል። ‘በናቴኮ ሴት ነኝ’ በሚለው መጽሐፉ ስንኞች እንምዘዝ! …. ግማሽ አካሏ ወንድ በትምክህት ቢከዳት ጧ! ብላ አለቀሰች አዛኝ ቢደርስላት፣ … ብሶት ተጫጭኗት ምንም ሰው አልሆነች በቀቢጸ ተስፋ ሕላዌንም ጠላች ያገሬ ጭቁን ሴት መድኅን መላ ያጣች….! ‘ሔዋንያት የትውልድ ፋብሪካዎች ናቸው፤ እነሱ ባይኖሩ ዓለም ባዶ ትሆን ነበር’ እንዲል ፈላስፋው ሶቅራጥስ። ስለሴት (ግማደ ሰቧ ፍጡር) ግፍና በደል ገሞራው እንዲህ ይላል። “መራራ ጭቆና በሰፈነበት ምዝብር ሕብረተሰብ ውስጥ ታፍነው የሚኖሩ ሔዋንያት ብሶታቸው፣ ፍዳቸው፣ በደላቸው፣ ጭንቀታቸውና መከራቸው እንደ ሰማዕታት ገድል እጥፍ ድርብ ነው…. አጉል ልማድ፣ ኋላቀር ባሕልና አድሃሪ ሕገ-ማኅበረሰብ ከከንቱ አስተሳሰቦች ጋር ተዳምሮ በአንድነት በመመሳጠር ዘርዓ ሔዋንን ሲጫወቱባቸው ሲያሾፉባቸው ኑረዋል” (ገጽ-23) በሥነ-ሕይወት ሳይንስና በትምህርተ-ጄነቲክስ (አካለ ሕላዌ) ሴቶችን ከወንዶች የሚያሳንስ ምንም አይነት አካላዊ ተሰጥኦ እንደሌለ ተረጋግጧል። ታሪክና ተረክ ግን ወገንተኛ መሆኑን ገሞራው ይናገራል። ተረክና ተረት አልባሌ ታሪክ የሚፈጥሯቸው አርበኞች ሁሉ በፆታቸው ተባዕት በመሆናቸው፤ በሴቶች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ በማሳደሩ ሊኖራቸው የሚችለው ዕድገት ላይ ትልቅ ደንቃራ ሆኖ መቆየቱን ይገልጻል። “የታሪክን ሁኔታዎችን የመመንዘር ትርጓሜያዊ አንጻር የታሪክን ትዕይንቶች ብንመረምር አንደርድሮ የሚያደርሰን ሴቶች ከወንዶች የከፋ ባህሪያዊ ድክመት እንዳለባቸው ከሚያሳይ ሥዕል ላይ ነው።” በሚት(ተለጣጭ ተረክ) ላይ የሚራቀቁት አቶ ቴዎድሮስ ገብሬ (በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፎክለር መምህር) ‘ተረኮች እማዊ ሳይሆን አባዊ ናቸው’ በማለት ይህን ጉዳይ ያጠናክሩታል። “በሚት ውስጥ ገነው ከሚታዩ አበይት ማኅበራዊና ባህላዊ እውነታዎች መሃል አንዱ ፆታዊ ወገንተኝነት ነው። የሰማናቸው፣ ያነበብናቸው ሚታዊ ተረኮች በእጅጉ አባዊ ለሆኑ ሥርዓቶች (ፓትሪያርካል ሲስተምስ) ያደሩ፣ በአብዛኛው በተባዕት ተጋዳሊያን የተሞሉ ናቸው” ይላል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዶክተር ይሁኔ (በገፅ-401) ስለሰው ማንነት ቀረጻ በተመለከተ ከጥንት እስከ ዛሬ አከራካሪ የሆኑ ፈላስፎችን ክርክር ያነሳሉ። ይኸውም የሰው ልጅ ‘ማን ቀረጸኝ? ተፈጥሮ ወይስ ተሞክሮ?’ የሚለውን መከራከሪያ ጽንሰ-ሃሳብ ይፈትሻሉ። በዚህም “ሰዎች ሲፈጠሩ የሰውየውን ችሎታ ይዘው ነው” እና “የሰዎች ማንነት የሚቀረጸው ከውልደት በኋላ በተሞክሮ ወይም ከአካባቢ ጋር በሚኖራቸው መስተጋብር ነው” የሚሉትን ሃሳቦች ወስደው ከእናት ሚና ጋር ያዛምዱታል። እናም እናት ‘በየትኛውም መደብ ልጅን አሳምራ ትቀርጻለች’ የሚል ድምዳሜ ሰጥተዋል። “በየትኛውም መንገድ በሰው ልጅ ላይ የእናት ቀራፂነት ስለሚኖር ከተጽዕኖዋ ማምለጥ የሚቻል አይመስለኝም።… አካባቢም ሰውን ይሰራዋል የሚሉትም ከውልደት በፊትም ሆነ በኋላ ከተፈጥሮ ጋር የሚደረገው ውስብስብ መስተጋብር ‘ሰው’ በመሆን ላይ ጉልህ ሚና ይጫወታል” ይላሉ። በዚህ እሳቤ ሰው የወላጆቹም፤ የአካባቢውም ውጤት መሆኑን በግልጽ እንረዳለን” ይላሉ። ሴቶች ከጥንት እስከ ዛሬ በኢትዮጵያ ማኅበረ-ባህላዊ እንዲሁም ለሰላምና ዕርቅ እሴቶች ጉልህ ሚና አላቸው። ሴቶች ያልተሳተፉበት ዘርፍ የለም። ከመሪነት፣ ጥበበኝነት፣ ከአገር ድንበር ጠባቂነትና የዲፕሎማሲያዊ ሚና… መጥቀስ ይቻላል። ሴቶች በሁሉም ማኅበረሰብ ዘንድ በሰላምና ግጭት አፈታት ግንባር ቀደም ተሰሚነት አላቸው። ለአብነትም ሀደ ሲንቄ፣ በሶማሌ-ሔር፣ በሲዳማ-ያካ፣ በራያ ማኅበረሰብ ዱበርቲዎች፣ በስልጤ-ሴረን ባህል መጥቀስ ይቻላል። ከሰሞኑ ባከበርነው የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ሴቶች ውለታ በወፍ በረር ማውሳት ይቻላል። የኢትዮጵያ ሴቶች ከሌላው ዓለም ሴቶች በተለየ የራሳቸው ቀለም ያላቸው፣ የአመራር ልምድ ያዳበሩ፣ የመወዳደሪያ ስነ-ልቦና ያላቸው፣ ችለው አሸንፈው ያሳዩ ናቸው። ሴቶች ድሉን በማስመዝገብ የተጫወቱትን ሚና ያህል፣ ገድላቸው በታሪክ በሚገባ አልተወሳም። ዶክተር አልማው ክፍሌ የተባሉ የታሪክ ምሁር በአንድ ወቅት ሚዲያ ላይ ቀርበው “በአድዋ ጦርነት ዘማቾች 75 በመቶ ሴቶች ነበሩ” ሲሉ ሰምቻለሁ። በአድዋ ጦርነት ሴቶች በተለያዩ ሙያዎች ተመድበው ከካምፕ እስከ ጦር ሜዳ ከመመገብ እስከ ማጀገን፣ ከማከም እስከ መዋጋት ድንቅ ሚና ተወጥተዋል። ድርብ ድርብርብ ኃላፊነት ይዘው የዘመቱ፣ ለወንዶችም ልብ፣ ሞራልና ወኔ አቀባዮች ነበሩ። እቴጌ ጣይቱን መሰል የአድዋ ሴት የጦር ፊታውራሪዎች በርካታ ናቸው። ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ ወልደአረጋይ ‘ታሪክ ዘመን ዘዳግማዊ ምኒልክ’ በተሰኘው መጽሐፋቸው የሴቶችን ሚና በተመለከተ እንዲህ ይላሉ፡- “እንዲህም እየሆነ፣ አጤ ምኒልክ ባዳራሹ እቴጌ ጣይቱ በእልፍኝ ባለሟሎችዎን ወይዛዝርቱን ይዘው ግብሩ አንድ ቀን ሳይጎድል፣ ይዘምታሉ። ከዘመቻ ላይ ጠጁ ማሩ አለመጉደሉ፣ ስለምንድነው ያልህ እንደሆነ ይህን ታሪክ መመልከት ነው። በስድስት ድንኳን እንጀራው ሲጋገር ሲያድር፣ በአራት ድንኳን ወጡ ሲሠራ ሲያድር፣ ጠጁ በቀንድ በኮዳ ደግሞ ሦስት መቶ ስድስት መቶ የሚሆን ገንቦኛ ሲጓዝ ግብሩ ይጎድል ይመስልሀል” (ገጽ-241) ደራሲ በዕውቀቱ ሥዩም ‘ከአሜን ባሻገር’ በተሰኘ መጽሐፉ ‘ሴቶች በዋሉበት’ በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ሴቶች ተጋድሎና ሚና “ከቁስ ባሻገር ከልብ ያቀርባሉ” ይላቸዋል። “ሴቶች ባዋላጅነት ከነበራቸው የማይተናነስ ሚና በጦር ሜዳ ተጫውተዋል። እናቶቻችን በጦር ወቅት፣ መሳሪያ ያቀርቡ ነበር። ምግብ ያቀርቡ ነበር። ሃሳብ ያቀርቡ ነበር። ልብ ያቀርቡ ነበር። ደስታ ያቀርቡ ነበር። ኧረ ምኑ ቅጡ። ሴቶች ባንድ በሙቀጫ ዙሪያ፣ ማኅበረሰቡን ኬሚስት፣ ገጣሚና የፖለቲካ ተንታኝ ሆነው ማገልገላቸውን ልብ እንበል” ይላል። (ገጽ-138) ዶክተር ይሁኔ (በገጽ-14) በበኩላቸው እናቶችን ሩህሩሆች፣ አጉራሽና አልባሽ፣ የችግር ቤዛዎች፣ ሕይወት ዑደት አስቀጣዮች፣ የሕይወት መድኅኖች፣ ባለብዙ ጸጋዎች፣ መልካም ባህሪ አውራሾች፣… በማለት ገልጸውታል። መላ ሴቶችንም በእናቶች አተያይ ማየት እንደሚገባም እንዲሁ። “እናትነት መልካም ገጽታዎችን ደራርቦ የያዘ የሴት ልጅ ትልቅ መገለጫ ነው። እናትነት ከፍ ያለ ሥልጣን ነው። እናትነት ጥልቅና ሰናይ ባህሪያት የሚፈልቁበት ምንጭ ነው። እናትነት የደግነት፣ የጥራት፣ የልህቀትና ተፈላጊነት ማሳያ ተምሳሌት ነው። እናትነት ሞት የማያደበዝዘው ኃያል መንፈስ ነው። እናትነት ከባድ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነው። … እናትነት የሰላም፣ የመልካም ግንኙነትና እንክብካቤ መፍለቂያ አድባር ናት። እናትነት ሰፊና ጥልቅ የሕይወት ትምህርት ቤት ነው። እናትነት ሌሎች ከስቃይ ነፃ እንዲሆኑ፣ ምቾት እንዲሰማቸው በሚደረግ ትግል ውስጥ ዋጋ እየከፈሉ መኖር ነው” በመቀጠልም የኢትዮጵያ እናቶችን ‘ጠቃሚ ነገር ሰጪዎች’ ይላቸዋል። “እናቶች ሰው የመሆኛ ቅመሞች የሚጨለፍባቸው ባህር ናቸው። … ሕይወታዊ ስሪታችን ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን የወሰደው ከእናት ነው። ከእናት የምናገኘው ‘ማይቶኮንድሪያ’ (ማይቶኮንድሪያ የኃይል ማመንጫ ክፍል ሲሆን የምንመገበው ምግብ እየተቃጠለና ወደ አስፈላጊው ኃይል እየተቀየረ ሕይወትን ያንቀሳቅሳል) የምግብ ማቃጠያ ምድጃ ወይም ኃይል ማመንጫ ቤት ሆኖ ያገለግላል። … ብዙ መልካም ስብዕና መገለጫዎች ምንጫቸው የእናት ፍቅር፣ የመልካም ስብዕና እና የርህራሄ ምንጭ ነው” (ገጽ- 61) ኢያሱ በካፋ ‘የኢያሱ በካፋ ወጎች’ በተሰኘው መጽሐፉ እናትነትን ማህጸንን፣ ምግብን፣ ትንፋሽን፣ ደም፣ ሥጋን እና ነፍስን ሰጥተው በረቂቅ ተፈጥሮ ሰውን ከመውለድ ባለፈ ፍቅራቸውን ዘላለማዊ ገደብ አልባ እና ዕልቆ-ቢስ እንደሆነ እንዲህ ገልጾታል። “እናትነት ነፍስን ማካፈል ነው፤ እናትነት የማይደበዝዝ ዘላለማዊ ፍቅር መስጠት ነው፤ እናትነት ከራስ ሕልውና ይበልጥ ለልጅ ማሰብ ነው፤ እናትነት ፍፁም ወረት አልባ መሆን ነው። እናት ለልጇ ያላት ፍቅር አይነጥፍም፤ አይለወጥም። ለእናት ልጇ ሁሌም ልጇ ነው” (ገጽ-4) እናትነት በቃላት ለመግለጽ እንደሚከብድ፤ በውለታ ማካካስ ይከብዳል። የእናት ውለታዋን መክፈል የሚችል ልጅ የለም። የእናት ፍቅርን ለመግለጽም በርካቶች አንደበታቸው ይተሳሰራል፤ ቃላት ይነጥፍባቸዋል፤ ስሜታቸውን መግራት ይሳናቸዋል። ድምፃዊ እሱባለው ይታየው(የሺ) ‘ይናገራል ፎቶ’ በሚል እናትና አባቱን በገለጸበት ሙዚቃ የመጨረሻው ማጠንጠኛው ‘እወድሻለሁ/እወድሃለሁ’ ያለው፤ እንዲሁም ድምፃዊት ብዙነሽ በቀለ ‘እናት ውለታዋ’ በተሰኘ ዘፈኗ ውስጥ (ዜማና ግጥም ጋዜጠኛ ሰለሞን ተሰማ)፤ “ወላጅ እናት እኮ ፍፁም በመንፈሷ፣ ልጇን ትወዳለች አብልጣ ከራሷ” እያለች በሚስረቀረቅ ድምጿ የምታንጎራጉረው ለዚህ ይመስላል። ዕውቁ የቋንቋ ሊቅ የሻው ተሰማ (የኮተቤው) ‘የጥቁር አፈር ትሩፋቶች’ በተሰኘው መጽሐፉ (ገጽ-79) ‘መቀነትሽን አጥብቂ’ በሚል ርዕስ ባሰፈረው ረዘም ያለ ግጥም ሁለት አንጓዎች ብቻ ስንመዝ የእናትነት ውለታን መመለስ እንደሚሳን፤ የእናትነት ግብሯ ‘እናት’ የሚለው ቃል በራሱ እንደሚያንስባት ያትታል። … “ለዚህ ወሮታሽ አጸፋ፤ እናት ይልሻል አገሩ፤ እኔም እናቴ ብልሽ መች ሊመጥንሽ ዳሩ። … እናትነት ምጡቅ ነው፤ እናት ከመባል ይልቃል፤ የግብርሽ ስንክሳር ዚቁ፤ በስያሜ መች ያልቃል”… በማለት ይገልጸዋል። መውጫ ዶክተር ይሁኔ የሴት እና እናትን የነገዋን መንገድ ከሳይንስ አተያይ አንጽረው፤ ከማኅበረ-ፖለቲካ፤ ከማኅበረ-ባህል ከፍታዋ አመሳክረው፤ እናትና ሀገርን መጋመድ አመስጥረው መልእክታቸውን እንደ መውጫ አስፍረዋል። ለስንበት አንድ አንቀጽ እንወርውር!! “የእናት ሀገር ህልውና ከእናቶች ሕይወት ጋር በቀጥተኛ ተዛምዶ አለው። የሰመረ ትውልድ ሊቀጠል የሚችለው በጥሩ ሁኔታ በተገነባ የእናቶች አቅም ነው። የእናቶች አቅም ሲገነባ የራሳቸውን አቅም ያውቃሉ፤ ምርጫቸውን በራሳቸው ይወስናሉ፤ እንዲሁም ለሚመጣው ማኅበራዊ ለውጥ የራሳቸውን አሻራ ያሳርፋሉ። ስለሆነም የእናቶችን አቅም ማጎልበት ትውልድን ማጎልበት ነው። እናቶች ላይ መሥራት ትውልድ ላይ መሥራት ነው”  
ትንታኔዎች
የአየር ንብረት ፋይናንስ-አፍሪካውያን ገፍተው ያልሄዱበት መንገድ
Feb 18, 2023 581
/በገዛኸኝ ደገፉ/ የአፍሪካ ቀንድ ከ40 ዓመታት ወዲህ ተከስቶ አያቅም የተባለለትን የድርቅ አደጋ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ ሆነዋል። የድርቁ አደጋ የከፋበት የአፍሪካ ቀንድ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ተሸክመዋል። በተጨማሪም የከተሞች መስፋፋትና የከተሜነት የኑሮ ዘይቤን እያስተናገደች ባለችው አፍሪካ የኃይል እጥረት፣ በቂ የመሰረተ ልማት አውታሮች ዝርጋታ አለመኖር፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት፣ ሥራ አጥነት ብሎም የወንጀሎች መስፋፋት አሕጉሪቱን ክፉኛ እየፈተኗት ይገኛሉ። የገጠር መሬት ምርታማነት መቀነስ ከገጠር ወደ ከተማ ለሚደረገው ፍልሰት አንደኛው ገፊ ምክንያት ሲሆን ለመሬቱ ምርታማነት መቀነስ ሰበብ ተደርጎ በዋናነት የሚጠቀሰው ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት የሚወልዳቸው የውኃ ኃብት መቀነስና ለተከታታይ ዓመታት የሚዘልቁት የድርቅ አደጋዎች መሆናቸው ጉዳዩን ይበልጥ አወሳስቦታል። እንደ አህጉር ከ4 በመቶ ያነሰ የካርቦን ልቀት ያላት አፍሪካ 65 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ መሆን ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። ከዚህ ችግር ሙሉ ለሙሉ መውጣት ባይቻልም ትርጉም ባለው ደረጃ መቀነስ እንዲቻል አህጉሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ኃብትና ወጣት የሰው ኃይል በማስተሳሰር ለውጥ ማምጣት ግድ ይላታል። በአፍሪካ የማይቀረውን የከተሞች መስፋፋትም ሆነ የህዝቦቿን የመልማትና የመለውጥ ፍላጎት ማሟላት ካለባት የአየር ንብረት ፋይናንስን የበለፀጉ ሀገራት ገቢራዊ ሊያደርጉት ይገባል። የአየር ንብረት ፋይናንስ (Climate Finance) የአካባቢ፣ ብሔራዊ ወይም ድንበር ተሻጋሪ ፋይናንስን የሚመለከት ሲሆን ከሕዝብ፣ ከግል እና ከአማራጭ የገንዘብ ምንጮች የተውጣጣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለማስተካከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ስምምነት ነው። የኪዮቶ ፕሮቶኮል እና የፓሪስ ስምምነት ደግሞ ሰፊ የገንዘብ አቅም ካላቸው አገራት አነስተኛ የኃብት አቅም ላላቸው እና ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ አገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ስምምነት ነው። ስምምነቱ “የጋራ ግን ደግሞ ልዩነት ያለው ኃላፊነትና አቅም” በሚለው መርህ መሰረት ያደጉ አገሮች አዳጊ አገራትን ለመርዳት የገንዘብ ምንጮችን እንዲያቀርቡ ይጠይቃል። ፋይናንሱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ወሳኝ ድጋፍ እንደሚሆን ታምኖበታል። ምክንያቱም ልቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ላቅ ያለ የኢንቨስትመንት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ። በተመሳሳይ ከአሉታዊ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎች ጋር ለመላመድ እና ተለዋዋጭ ጫናዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ይጠይቃል። ከጥቂት አሥርት ዓመታት በፊት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበው የምእተ ዓመቱ የልማት ግብ ሰነድም ሆነ በቅርቡ በሚጠናቀቀው ዘላቂ የልማት ግቦች ላይ ለጉዳዩ ከፍ ያለ ትኩረት ቢሰጠውም እስካሁን ግን የፈየደው ነገር የለም። አፍሪካ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችን ለመላመድ ዓመታዊ 41 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የፋይናንስ ክፍተት ይገጥማታል። ይህን ክፍተት ለመሙላት አዲስ አበባ እያስተናገደች ባለችው 36ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ የአየር ንብረት ፋይናንስ ገቢራዊ ማድረግን ቀዳሚ ትኩረታቸው መሆን እንዳለበት የአንድ ዘመቻ (ONE Campaign) አጽንኦት ሰጥቶ ምክረ ሃሳቡን ሰንዝሯል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የአንድ ዘመቻ ዳይሬክተር ዶሪን ኒኒናሃዝዌ የአፍሪካ መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመላመድ ፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥን አስከፊ ተጽዕኖ የመቋቋም አቅም እንዲገነቡ መክረዋል። አፍሪካ ባልፈጠረችው የአየር ንብረት ለውጥ ህዝቦቿ ለከፋ ጥቃት እየተዳረጉ ይገኛሉ። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች የበለጸጉ አገሮች የገቡትን የማላመድ ፋይናንስ ድጋፍ ቃል እንዲፈጽሙ ከማግባባት ባለፈ ማሳሰብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይህ ማለት እኤአ ከ2020 እስከ 2025 በዓመት 100 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመተውን ግብ የማሳካት ተግባር የሚጠይቅ ነው። ከዚህ ባሻገር በቀጣዮቹ ዓመታት በተጨመሩ መዋጮዎች የሚስተዋሉ ጉድለቶችን መፍታት እና በግብጿ ሻርም ኤል ሼክ ከተማ ባስተናገደችው COP-27 ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ለመላመድ በእጥፍ ፋይናንስን የማቅረብ ቁርጠኝነት የማቅረቢያ ዕቅድ ሊነድፉ ይገባል ነው ያሉት። የአፍሪካ አገሮች ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ከሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ጋር ሲታገሉ ቢቆዩም አሁን ላይ “አፍሪካ በአፈፃጸሙ ላይ መጠነኛ መሻሻል አሳይታለች” ብለዋል። እናም በ36ኛው የመሪዎቹ ጉባዔ የተገኙ ስኬቶች እና የጠፉ ዕድሎች እንዲሁም የድርጅቱን ዓላማዎች ለማሳካት በአየር ንብረት ፋይናንስ በጥልቀት መክረው ለተሻለ ስኬት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዋና ዳይሬክተር አንቶኒዮ ቪቶሪኖ በአየር ንብረት ምክንያት የሚፈጠሩ መፈናቀልን ለመግታት የተሻሻሉ የመላመድ እና የተጽዕኖ ቅነሳ ተነሳሽነት ገቢራዊ ለማድረግ በአገራት መካከል ጠንካራ አጋርነትን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ያሰምሩበታል። በተለይ በአፍሪካ ቀንድ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ኑሯቸውን መሰረት ባደረጉ ህዝቦች ላይ አውደ-ተኮር መላመድ እና የመቋቋም አቅም ግንባታ መፍጠር ይገባል። ለዚህ ደግሞ መላመድን የሚደግፉ ፋይናንስ ለማግኘት የሚረዱ መመሪያዎች ይበልጥ የተፍታቱ መሆን ይኖርባቸዋል ሲሉ ቪቶሪኖ ይሞግታሉ። ከ 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በተጓዳኝ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ (High-Level Forum) ላይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በሻርም ኤል ሼክ በተካሄደው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መላመድን፣ መከላከልን እና ዝግጁነትን ለማሻሻል ዓለም አቀፍ ትብብር ማጎልበት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አውስተዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥን አስመልክቶ ያወጣቸው የስምምነት ማዕቀፎች (United Nations Framework Convention on Climate Change (UNFCCC)) በርካታ ዝርዝርና ሚዛናዊ አካሄዶችን የያዙ ናቸው። ያም ሆኖ አተገባበራቸው እዚህ ግባ የማይባል በመሆኑ የሚታሰበውን ያህል ለውጥ ማምጣት ሳይችል ቀርቷል። በዚህም ቦረና ዞንን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የአየር ንብረት መዛባት፣ የሙቀትና የባህር ጠለል መጨመር፣ ጎርፍ፣ ድርቅ እንዲሁም ያልተገመቱ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ዓይነተኛ አማራጭ እንደሆነ ብዙዎቹ ይስማሙበታል። ዳሩ ግን አገራትን፣ አህጉርን፣ ዓለምን እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ግዙፍ ኩባንያዎችን ያስተሳስራል የተባለለት የአየር ንብረት ፋይናንስ በቅጡ ገቢራዊ ማድረግ ባለመቻሉ የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በርካታ ህዝቦች ዳፋውን ለመጋፈጥ ተገደዋል። የአየር ንብረት ፋይናንስን በመተግበር በመስኩ የተጎጂዎችን ቁጥር ሊቀንሱና የዓለምን ሥነ-ምህዳር ከተቻለ ወደ ቀድሞው ሊመልሱ አሊያም አሁን ባለበት አረጋግተው ሊያቆዩ የሚያስችሉ በርካታ አማራጮች ተግባራዊ ሊደረጉ ይገባል። ለአብነትም ለድሃ ሃገራት አርሶ አደሮች የግብርና ምርቶች ተገቢውን ዋጋ በመክፈል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን እንዲቋቋሙ ማድረግ ከአማራጮቹ መካከል አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግዙፎቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሚያስወግዷቸው በካይ ጋዞች ተመጣጣኝ የጤና ሥርዓት በመዘርጋት የታዳጊ ሃገራት ዜጎችን የጤና አገልግሎት ማሻሻል ሌላው አማራጭ ነው። የተፈጥሮ ኃብቶችን የሚጎዱ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ተፈጥሮን በሚንከባከቡ ዘዴዎች መተካት እንዲሁም ብክለትን የሚያስቀሩ የምርት ሂደቶች መለማመድ ጥቂቶቹ የመፍትሄ አማራጮች ተደረገው የሚወሰዱ ናቸው። በፓሪስ ከተደረሰውን የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ቀደም ብሎ በፈረንጆቹ 1994 ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም (Global Environment Facility-GEF) COP-16 ዓለም አቀፍ ጉባዔ በኋላ በ2010 አረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ (Green Climate Fund-GCF) እንዲሁም በ2001 ደግሞ ልዩ የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ (Special Climate Change Fund-SCCF) እና የመላመድ ፈንድ (Adaptation Fund-AF) የተባሉ ማዕቀፎች የተዘጋጁ ቢሆንም ስለጉዳዩ የሚያስረዱ ተከታታይ ስብሰባዎች ከማዘጋጀት በዘለለ ብዙ ርቀት መጓዝ ሳይችሉ ቀርተዋል። በቅርቡ በአለም ባንክ አሰባሳቢነት በኬንያ ናይሮቢ ተዘጋጅቶ በነበረው የአህጉሪቱን መሪዎች ባለሃብቶችንና ምሁራንን ባካተተውና “One Planet Summit” በተሰኘ መሰል ጉባዔ ላይም አፍሪካውያን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚገጥማቸውን ችግሮች ተከላክለው ሁለንተናዊ ዕድገታቸውን እንዲያፋጥኑ ካስፈለገ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምጣኔ ኃብት ፖሊሲ አዘጋጅተው መተግበር እንደሚኖርባቸው መግባባት ላይ የተደረሰ ቢሆንም አሁንም ጥያቄ ያስነሳው አፈጻጸሙ ስለመሆኑ ብዙ ተብሎለታል። ክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ የተባለ ድርጅት ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያመለክተው አፍሪካ እንደ ፈረንጆቹ የጊዜ ቀመር ከ 2020 እስከ 2030 ባሉት አሥር ዓመታት 2 ነጥብ 8 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር አሊያም በየዓመቱ ከ2 መቶ ሃምሳ ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያስፈልጋት ሲሆን አህጉሪቱ ከዘርፉ እያገኘችው ያለው ገንዘብም ከሚያስፈልጋት 12 በመቶውን ወይም 30 ቢሊየን ዶላር ብቻ ስለመሆኑ አስነብቧል። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው ሊሰሩ የሚችሉ በርካታ ተግባራት እንዳሏት የሚያትተው ሪፖርቱ ከአየር ንብረት ፋይናንስ የሚገኘው ገንዘብ በትራንስፖርት፣ በኃይል ልማት፣ በኢንዱስትሪ ብሎም በግብርና፣ በአፈርና በደን ኃብት አጠቃቀም ውጤታማ በሆነ መንገድ ከዋለ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ኃብቶች መንከባከብ ከማስቻሉም ባለፈ ላቅ ያለ ፋይዳ ይኖራዋል ብሏል። ይህ ሲሆን የሥራ ዕድል በመፍጠር የሥራ አጥ ቁጥርን በመቀነስ ለአህጉሪቱ ሰላምና መረጋጋት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖው ያስረዳል። ላለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ገቢራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራን የማስፋፋትና የተጎዱ አካባቢዎችን የማከም ሥራ እንዲሁም አይቀሬ የሆኑትን ከተሜነትና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ታሳቢ ያደረጉ የአየር ንብረት ፖሊሲዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ለአፍሪካ ሃገራት እየፈጠረው ያለው በጎ ተጽዕኖ በግልጽ እየታየ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ጥረት ግን በአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲደገፍ አገራዊና የተቀናጀ አሕጉራዊ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል። ከአጠቃላይ የአፍሪካ አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ግብጽ ብቻ 151 ቢሊየን ዶላር ከአየር ንብረት ንብረት ፋይናንስ ማግኘት እንደሚኖርባቸው የክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ ሪፖርቱ ይገልጻል። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በመጭው የCOP-28 ጉባዔ የራሷንና የአፍሪካን ፍላጎት የሚያስጠብቁ የፋይናንስ ትልሞችን የመንደፍ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባታል፡፡ የ COP-27 ጉባዔ ለአፍሪካ ያስገኘውን ውጤት እና አንድምታ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የመሪዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ እና አስተባባሪ በሆኑት በኬንያው ፕሬዝዳንት ሰብሳቢነት በኅብረቱ የአዲስ አበባ ጉባዔ ላይ በጥልቀት ይገመግማል ተብሎ ይጠበቃል። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ ጥረቷን የሚያጎለብት የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ጠንካራ ተሳትፎ ልታደርግ ይገባል። የአፍሪካ አገራት ገፍተው ረጅም ርቀት ያልሄዱበት የአየር ንብረት ፋይናንስ እና ሌሎች የድጋፍ አማራጮችን በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት በመጠቀም የአየር ንብረት ተጽዕኖን የሚቋቋሙበት ጠንካራ አቅም ሊገነቡ ግድ ይላቸዋል። በእርግጥም አፍሪካውያን መሪዎች በሚያደርጉዋቸው ስብሰባዎች በየማዕዝናቱ በድርቅ ሳቢያ ለምግብ እጦት የተዳረጉ ህዝቦቻቸውን የሚታደጉበት ሁነኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበትን ዘዴ ነድፈው ረጅም ርቀት ሊጓዙ ይገባል። ”
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 547
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ - የአፍሪካ የዘመናት ፈተና
Feb 13, 2023 551
በረከት ሲሳይ በርካታ የአፍሪካ አገራት ነፃነታቸውን ከተቀዳጁበት ከ1960ዎቹ ጀምሮ እስካሁን እልባት ካልተገኘላቸው አፍሪካዊ ጉዳዮች መካከል ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ አንዱ ነው። ለዚሁ ጉዳይ በርካታ መነሾ ቢኖሩትም ቅኝ ግዛቱ የፈጠራቸው ፖለቲካዊ ስንጥቃቶች፣ ድህነትና ሌሎች ማኅበራዊ ምስቅልቅሎሽ ለእነዚህ የጸጥታ ችግሮች በአብዛኛው የሚነሱ ምክንያቶች ናቸው። በአህጉሪቱ ላለፉት 40 እና 50 ዓመታት መቋጫ በሌለው መልኩ እዚህም እዚያም የሚነሱ ግጭቶችና ጦርነቶች ለአያሌዎች ሞትና የአካል ጉዳተኝነት ለገሚሱ ደግሞ ለዘመናት ከኖረበት ቀዬ እንዲሰደድ ምክንያት ሆነዋል። በብዙ ጥረት የተገነቡ መሰረተ-ልማቶች ወደ ፍርስራሽነት እንዲለወጡና በሂደት ላይ ያሉ የዘመናዊ አገር ግንባታ ሂደቶች እንዲስተጓጎሉና በፈተናዎች እንዲታጀቡ አድርጓል። ይህንኑ ኢኮኖሚያዊ ኪሣራ በሚያሳይ መልኩ፤ የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ከሁለት ዓመታት በፊት ያወጣው ሪፖርት እንደሚያሳየው፤ በአፍሪካ የሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮች በየዓመቱ የአገራቱን አጠቃላይ አገራዊ ምርት (ጂ ዲ ፒ) እድገት ከ4 በመቶ እስከ 6 በመቶ እንዲቀንስ ያደርገዋል ይላል። በተለይም ደግሞ በኢኮኖሚው ላይ የሚከሰቱ ችግሮች ተጽዕኖ ዓመታትን የሚዘልቅ በመሆኑ ተደራራቢና ድግግሞሽ ያሏቸው ችግሮች እንዲበራከቱ በር ከፍቷል። በእነዚህ ድርብርብ ውጥንቅጦች በአህጉሪቱ በከባድ ድህነት የሚኖሩ ዜጎች ህይወት ይበልጡኑ እንዲወሳሰብባቸውና ለከፋ ማኅበራዊ ችግር እንዲጋለጡ እያደረገ ነው። ከዚህም ባለፈ የጸጥታ ችግሮች በአፍሪካ ሳያባሩ መቀጠላቸው ዛሬም ጉዳዩን በአንክሮ እንድንመለከተው ያስገድደናል። ይህንን በሚያስረግጥ መልኩ ያለፈው የፈረንጆች ዓመት (2022) ግጭቶች የተስተዋሉበት ዓመትና በዘንድሮ ዓመት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩ ተመላክቷል። በሰላም ስምምነት የተቋጨውን በኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረውን ጦርነት ጨምሮ እስካሁን እልባት ያልተገኘላቸው የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና የደቡብ ሱዳን የጸጥታ ችግሮች ተጠቃሽ መሆናቸውን ነው የአፍሪካ የደኅንነት ተቋም ሪፖርት የሚያሳየው። ከዚህ ጎን ለጎን በሳሀል፣ በቻድ ሃይቅ ሸለቆ፣ በምስራቅ አፍሪካና በሰሜን ሞዛምቢክ ጸጥታን የሚያውክ የጽንፈኝነት እንቅስቃሴ መኖሩንም አመላክቷል። ከዚህ ጎን ለጎን በቡርኪና ፋሶ፣ በጊኒ፣ ማሊ፣ ሱዳን፣ ቻድ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ጅቡቲ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ማዳጋስካርና ኒጀር የተሳካና ያልተሳካ የመፈንቅለ-መንግሥት (ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ) ሙከራ መካሄዱንና የፖለቲካ አለመረጋጋት እንደተስተዋለባቸው ነው ሪፖርቱ ያወሳው። መንግሥታዊ የአስተዳደር ግድፈቶች፣ ምርጫን ተከትሎ የሚቀሰቀስ አለመግባባትና ሌሎችም በአህጉሪቱ ላለፉት ሁለት ዓመታት የተከሰቱ የጸጥታና የደኅንነት ችግሮች ለተያዘው የፈረንጆች ዓመትም ትልቅ ሥጋት መሆኑን ነው ያነሳው። አፍሪካ ኅብረት በበርካታ አገሮች የጸጥታ ችግሮች እንዲቆሙና እንዲረጋጉ በማድረግ አዎንታዊ ሚና መጫወቱ ተገልጿል። ለአብነትም በኢትዮጵያ በዘላቂነት ግጭትን ለማቆም የተደረሰው የሰላም ስምምነት ተጠቃሽ ሲሆን በሌሎችም አገራት ወደ ተሻለ ፖለቲካዊ መረጋጋት እንዲመጡ ትልቅ ሥራ ሰርቷል። ይህም ሆኖ አሁንም ድረስ ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ በኩል በርካታ ሥራ እንደሚቀር ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ በምዕራብ ሳሀል ያለው ከአልቃይዳና ከአይ ኤስ ጋር ግንኙነት ያለው ጽንፈኛ ቡድን በአካባቢው የፈጠረው አለመረጋጋት፣ ከማሊ የፈረንሳይ ጦር መውጣትና ማሊ ራሷ ከሳሀል ቡድን አምስት የጸጥታ መዋቅር መውጣቷም ሌላው የአህጉሪቷና የአካባቢው ራስ ምታት ሆኗል። የቻድ ሃይቅ ሸለቆ አካባቢ (በኒጀር፣ ቻድ፣ በካሜሮንና ናይጄሪያ) የሚስተዋለው የቦኮሃራምና ሌሎች የጽንፈኝነት እንቅስቃሴ፣ በምስራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ራሱን ኤም23 በማለት የሚጠራው ቡድን ከማዕከላዊ መንግሥት ጋር ጦር መማዘዙ እንዲሁም በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው በመንግሥትና በተቃዋሚ መካከል የተቀሰቀሰው የሽምቅ ውጊያ አሁንም አለመቆሙ፤ የአፍሪካ ኅብረት ጸጥታን በተመለከተ በዚህ ዓመት ትኩረት ሊያደርግበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ነው የእንግሊዙ ቻም ሃውስ የተሰኘው የጥናት ተቋም መረጃ የሚያመለክተው። በተያዘው የፈረንጆች ዓመት በተለያዩ ደረጃ የሚካሄዱ 17 ብሔራዊ ምርጫ መኖራቸውንና ይህንንም ተከትሎ ሊከሰቱ የሚችሉ የድኅረ-ምርጫ ፖለቲካዊ ግጭቶችን በማስቀረት ረገድ አፍሪካ ኅብረት አዎንታዊ ሚና መጫወት እንደሚጠበቅበትም ተመላክቷል። የአፍሪካ ኅብረት ቀጣይ አቅጣጫስ? አፍሪካ ኅብረት በበርካቶች አይን ሲታይ ምንም እንኳን የፖሊሲና የስትራቴጂ ችግር ባይኖርበትም ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ በበርካታ ጉዳዮች ላይ ችግሮች ተስተውሎበታል። ለዚህም ተቋሙ ካለበት የፋይናንስና ሌሎች ተያያዥ የቴክኒክ ችግሮች በተጓዳኝ በዋነኛነት አባል አገራት በኅብረቱ ቻርተር በመመራት ረገድ በርካታ ክፍተቶች መኖራቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በተለይም በጸጥታና ደኅንነት ምክር ቤት በኩል የሚወስናቸው ስምምነቶች ገቢራዊ አለመሆናቸው ትልቅ ክፍተት ሲሆን ምክር ቤቱም በቅርቡ ያደረገው ስብሰባ ይህንኑ አጋልጧል። ይህም አፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ መልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲ እንዲጎለብት በማድረግ ረገድ ያለው ቁርጠኝነት ልዩ ትኩረት የሚሻ መሆኑን አመላክቷል። ለአብነትም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2020 የጥይት ድምፅ የማይሰማባት አህጉር ለመፍጠር ያቀደው ዕቅድ ምንም እንኳን ዕቅዱ ከጅምሩም ቢሆን ያለው ነባራዊ ሁኔታና የግጭቶች የመስፋፋት አዝማሚያ ከግምት በማስገባት ሊሳካ እንደማይችል በርካታ የመስኩ ተንታኞች ቢናገሩም ኅብረቱ በዚህ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት አልቻለም። ለዚህም ደግሞ በቀዳሚነት ምንም እንኳን የአባል አገራት የፖለቲካ ቁርጠኝነት ማነስ ትልቁን ድርሻ ቢይዝም የሚወስዳቸው እርምጃዎች ሳይሸራረፉ ተግባራዊ ለማድረግ መቸገሩን ነው የሚያሳዩት። በአፍሪካ በሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ሥራዎች በቁርጠኝነት መሥራት ይገባል። በተለይም ደግሞ አፍሪካ ኅብረት በቅርቡ ዳግም የከለሰውን በአህጉሪቱ የጥይት ድምፅ ለማጥፋት የወጣውን ፍኖተ- ካርታና እንዲሁም የክትትልና የግምገማ ማዕቀፍ ፈጥኖ ወደ ሥራ ማስገባት ይኖርበታል። ይህንንም ተከትሎ በጸጥታና የደኅንነት ምክር ቤቱ ያቋቋመውን የባለሙያዎች ቡድን የያዘ ማዕቀብ ለመጣል የሚሰራው ንዑስ ኮሚቴም በአግባቡ መጠቀም አለበት። አሁን ላይ በአህጉሪቱ ለጸጥታ መስፈን ሥጋት በሚሆኑና በሚያቆጠቁጡ ጉዳዮች ላይ እልባት ለመስጠት መረባረብ እንዳለበት ነው የሚጠቀሰው። በተመሳሳይ የሚወስዳቸው እርምጃዎችም በባህሪያቸው ተከታታይነትና ወጥነት ያላቸው እንዲሁም ችግሮች ከተፈጠሩ በኋላ ሳይሆን ከመፈጠራቸው በፊት አስቀድሞ መከላከልና ማክሸፍ ላይ ሊረባረብ እንደሚገባ ነው የሚያነሱት። ከዚህ በተጓዳኝ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማፋጠን የሚያስችሉ የአገራትን የፖለቲካ እንቅስቃሴ መደገፍና በዘላቂነት ዴሞክራሲ ባህል እንዲሆን የሚያስችሉ ሥራዎችን መደገፍ እንዳለበትም ነው የሚነሳው። በተለይም ደግሞ ወጣቶችን ያሳተፉ የዴሞክራሲ ግንባታ ሥራዎች በስፋት መሠራት እንዳለበት ነው የሚጠቀሱት። ከዚህ ጎን ለጎንም የአፍሪካ የእርስ በርስ መገማገሚያ መድረክም (ፒር ሪቪው ሜካኒዝም) በተለይም መልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲጎለብት በማድረግ ረገድም አበርክቶው ከፍ እንዲል መሠራት ይጠይቃል። የሰላም ሥራውን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችለውን የሰላም ፈንድም ማሰባሰብ እንዳለበትም ነው የሚነሳው። ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት አጋማሽ ላይ የሰላም ፈንዱ አጠቃላይ ገቢ 328 ሚሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 22 አባል አገራት ሙሉ በሙሉ እንዲሁም አምስት አገራት ደግሞ በከፊል የሚጠበቅባቸውን መዋጮ አዋጥተዋል። በሌላ በኩል 28 አባል አገራት ደግሞ መዋጮውን መክፈል አለመቻላቸውን ነው የአፍሪካ ኅብረት የሰላምና ደኅንነት ሪፖርት የሚያመለክተው። በመሆኑም አፍሪካ ኅብረት አባል አገራት የሚያዋጡትን ገንዘብ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እንዲጨርሱ ቅስቀሳ ማድረግን በአፍሪካ ጥላ ሥር በተለያዩ አገራት የሚያንቀሳቅሰውን የሰላም ሥራ ውጤታማ ማድረግ ይገባዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት(ተ.መ.ድ) የጸጥታ ምክር ቤት ጉዳይ ላለፉት 15 ዓመታት በአፍሪካ መሪዎች በስፋት የተቀነቀነው አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት ይገባል የሚለው ጉዳይም አፍሪካ ኅብረት በዘንድሮ ጉባዔው ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። ምክር ቤቱ ከሚመለከታቸው ጉዳዮች ውስጥ ከ70 በመቶ በላይ የሚሆኑት አፍሪካን የተመለከቱ መሆናቸውና ይህም ሆኖ በምክር ቤቱ ውስጥ አፍሪካ አለመወከሏ የፍትሃዊነት ጥያቄ ሲያስነሳ ቆይቷል። በርካታ የአፍሪካ መሪዎች እንዲሁም ኅብረቱን በሊቀ-መንበርነት የመሩት እስከ ወቅቱ ሊቀ-መንበር የሴኔጋሉ ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል ድረስ ጥሪያቸውን በተለያዩ መድረኮች አሰምተዋል። አሁን አሁን ላይም ጥያቄውን ምንም እንኳን የሩቅ ምስራቆቹ ጃፓንና ቻይና እንዲሁም ሕንድ አስቀድመው ቢቀበሉትም በተለይም አንዳንድ የምዕራብ አገራት ያሏቸውን የሃሳብ እቀባ በማንሳት ጉዳዩን እንዲጋሩት በማድረግ አፍሪካ ትልቅ ስኬት አግኝታለች። ይህም ሆኖ አሁንም አፍሪካ ስንት መቀመጫ ይኑራት? እንዲሁም ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ይሰጣት ወይስ አይሰጣት? የሚለው ጉዳይ ላይ ክርክሮቹ እንደቀጠሉ ነው። በዘንድሮ ጉባዔው ኅብረቱ በእነዚህ ጉዳይ ላይ ተወያይቶ ወደ መጨረሻ ምዕራፍ ላይ የሚደረስበትን ውሳኔ ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል። ይህንንም ማድረግ ከተቻለ በአፍሪካ ቀደምት መሪዎች ሲቀነቀን የቆየውን "አፍሪካዊ መፍትሔ ለአፍሪካ ችግሮች" የሚለውን ብሂል እውን ለማድረግና አህጉሪቷ ላይ ዘላቂ ሰላምና ደኅንነትን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ላይ አዎንታዊ አበርክቶ እንደሚኖረው ታምኖበታል።
ጠንካራ አንድነት - ለዘላቂ ሰላም መሰረት!
Feb 3, 2023 494
በእንግዳው ከፍያለው (ባህር ዳር ኢዜአ) በረጅም እንጨት ጫፍና ጫፍ በገመድ ታስረው የተንጠለጠሉ ቋጠሮዎችን ተሸክማ ከጓደኞቿ ጋር ገበያ እየሄደች ነበር የተገናኘነው። ወጣት ማሪማ ሜካ ትባላለች፤ ዕድሜዋ ከሃያ ዓመት አያልፍም። በእንጨቱ አንደኛው ጫፍ 10 ሊትር አረቄ የያዘ ጀሪካን፤ በሌላኛው ጫፍ ደግሞ ሌላ ቋጠሮ በማንጠልጠል ተሸክማለች። ሸክሙን በትካሸዋ ላይ ጣል እድርጋ ፈጠን እያለች ስትራመድ ላየ በፊቷ ላይ አንዳች የብርታትና የጽናት መንፈስን ያነባል። እንደእኔ ለአካባቢው እንግዳ የሆነ ሰው “ሴት ልጅ እንዴት ይህን ያህል ክብደት ተሸክማ ትጓዛለች?” ብሎ ራሱን ሊጠይቅ ይችላል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማንዱራ ወረዳ ነዋሪዋ ወጣት ማሪማ ግን ሸክሙ እንደ ኩበት ቀሏት ይሁን ጽናቱን ፈጣሪ ሰጥቷት ባላውቅም በደስታ ወደ ፊት መራመዷን ቀጥላለች። “የኛ ችግር የምንይዘው ሸክም ሳይሆን የጸጥታ ስጋት ነበር” የምትለው ወጣቷ ባለፉት ዓመታት በኛ ላይ የደረሰው አስከፊ ሰቆቃና መከራ ለጠላትም እንዲገጥመው አልመኝም በማለት ትናገራለች። ባለፉት ዓመታት በአማራና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች አዋሳኝ ወረዳዎች ሲከሰት የነበረው ግጭት የሁለቱን ክልሎች ህዝቦች ለሞት፣ ለስደት፣ ለንብረት መውደም እንዲሁም ለተለያዩ ችግሮች ዳርጓቸው መቆየቱ የቅርብ ትውስታ ነው። አካባቢው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚገነባበት፣ ሰፋፊ የእርሻ ኢንቨስትመንት፣ የስኳር ፕሮጀክቶችና ሌሎች የኢንዱስትሪ ልማቶች ያሉበትና ለመተግበር የታቀደበት በመሆኑ የውጭ ሃይሎች ግጭት እንዲነሳ እጃቸውን ሊያስገቡ እንደሚፈልጉ ሳይታለም የተፈታ ነው። ወጣት ማሪማ ግጭት በተከሰተባቸው በነዚያ አስከፊ ጊዜያት የነበረውን ሁኔታ፣ የደረሰውን ጉዳት፣ በተከፈለው መስዋዕትነት የመጣውን ሰላም በሚያስታውስ የተስፋ ስሜት "ጸረ ሰላም ሃይሎች ያስነሱት ግጭት ለዘመናት በአንድነት የኖረውን የሁለቱ ክልሎች ህዝቦች ተስፋ አጨልሞት ነበር፤ በሰላም እጦት ሁሉም ህዝብ ጫካ ገብቶ ኑሮውን ከዱር አውሬ ጋር ያደረገበት የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው" ትላለች። በአሁኑ ወቅት ጸረ ሰላም ሃይሎችና ተባባሪዎቻቸው የፈጠሩት ሰው ሰራሽ ችግር ሊፈታ መቻሉ እፎይታን መፍጠሩን ትገልጻለች። በወቅቱ ሕክምና፣ መድሃኒትና ሌሎች የጤና መጠበቂያ ቁሶች ባለመኖራቸው ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ በወባ እና ሌሎች በሽታዎች ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖች እንዳሉ በመጥቀስ፤ በአሁኑ ወቅት የጸጥታ አካላትና ሰላም ፈላጊ የአካባቢው ተወላጆች ከመንግሰት ጋር በመሆን ባደረጉት ጥረት የነበረው ግጭት ተወግዶ በአካባቢው ሰላም ሰፍኗል። ይህም ለማሪማና ለአካባቢው ነዋሪዎች እፎይታን በማጎናጸፉ በጣም ደስተኛ ናቸው። የተገኘውን ሰላም ተከትሎ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማንዱራ ወረዳ ተነስታ በአማራ ክልል አዊ ዞን ቻግኒ ከተማ በመምጣት ለመገበያየት በቅታለች። ከጓደኞቿ ጋር ከቻግኒ ከተማ የሚፈልጉትን ገዝተው ወደ አካባቢያቸው ወስደው በትርፍ ለመሸጥ ምቹ ሁኔታም ተፈጥሮላቸዋል። በቻግኒ ከተማ የቅዳሜ ገበያ የተለያዩ የንግድ እንቅስቃሴዎች ይካሄዳሉ። በርበሬ፣ የተለያዩ የጥራጥሬ፣ የቅባትና የአገዳ ምርቶች ለሽያጭ ይቀርባሉ። አልባሳት፣ የሴቶች ጌጣጌጥ እና የንጽህና መጠበቂያ ቁሶች እንዲሁም ሌሎች የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ንግድ ልወውጥ የሚካሄድባት ከተማ መሆኗን በነበረኝ የአጭር ጊዜ ቆይታ አስተውያለሁ። ገበያተኛው የተፈጠረውን ሰላም በማጣጣም ላይ መሆኑን በገበያው ውስጥ ከሚያሳየው መስተጋብር መረዳት ቀላል ነው። እኔም ይሄን በተደጋጋሚ ታዝቢያለሁ። ከህዝቡ ፊት ያነበብኩት በግጭቱ የተነሳ በደረሰው ችግር ምክንያት ቁርሾና ቂም በቀል ውስጥ መግባትን ሳይሆን የሰላምና እርስ በርስ መዋደድና የመደጋገፍ ስሜትን ነው። ይሄን ደግሞ በቻግኒ ከተማ በሚካሄደው የቅዳሜ ገበያ መስተጋብር ላይ ተገኝቶ ማረጋገጥ ይቻላል። ገበያው የሁለቱም ክልሎች ህዝቦች ያላቸውን ይዘው መጥተው በነጻነት የሚገበያዩበት ነው። አሁን በሰላም ተገበያይቶ ወደ ቤት የሚመለስበት ሁኔታ በመፈጠሩ ለወጣት ማሪማ እና እንደ እሷ ላሉ ወጣቶች ደስታና እፎይታን ሰጥቷል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የማንዱራ ሚሊሻ የሆኑት አንመይ አልቤም በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈጥሮ የነበረውን የሰላም መታጣት ችግር ዛሬ መፈታት በመቻሉ በነጻነት ያለስጋት ለመገበያየት መብቃቱን አስረድቷል። "ያ አሰቃቂና የእልቂት ጊዜ አልፎ ተገናኝተንና እርስ በርስ ተገበያይተን በሰላም ወደየቤታችን እንመለሳለን ብሎ ማሰብ እንደ ከንቱ ህልም ነበር" ይላል የነበረውን ሁኔታ ሲያስታውስ። “ሚሊሻ እንደመሆኔ ከፌዴራልና ከክልሎች የጸጥታ ሃይሎች ጎን በመሰለፍ ግጭት ቀስቃሾችን ለመፋለም ጨካ ለጫካ ያሳለፍነው ጊዜ መቼም አይረሳኝም” ያለው ሚሊሻ አንመይ፣ ስንቶች በሕክምና፣ በመድሃኒትና ምግብ እጦት ህይወታቸው ማለፉን አንስቷል። "አማሟቴን አሳምረው" እንደሚባላው በወጉ መሞትና መቅበር ትልቅ ጸጋ መሆኑን የገለጸው አንዳች የሀዘን ስሜት ውስጥ በመግባት ነው። አሁን ላይ ሁሉም የደረሰውን ጉዳት በመርሳት የተገኘውን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል እየተንቀሳቀሰ ነው። የሁለቱ ክልል ህዝቦች ቂም በቀልን ትተን በጋራ የምንሰራበት ወቅት ላይ መድረሳችን ህዝቡ ከጥንት ጀምሮ ያለው የመተሳሰብ፣ የአብሮነትና አንድነት የመንፈሰ ጠንካራነት ማሳያ እንደሆነም ነው የገለጸው። በእርግጥም የማንዱራ ሚሊሻው እንዳለው በአካባቢያቸው ትምህርት ቤቶች በመከፈታቸው ህጻናት ያለስጋት በመማር ላይ ናቸው። የጤና ተቋማትም የተለመደውን የሕክምና አገልግሎት እየሰጡ ነው። በሰላም እጦት ተዘግተው የነበሩ መንገዶች በመከፈታቸውም ሁሉም ተሯሩጦ ኑሮውን ለማሸነፍ ላይ ታች እያለ ነው። ባለሃብቶችም በክረምቱ በግብርናው መስክ ተሰማርተው ማልማት ችለዋል። የጸጥታ ስጋት ተወግዶ ሌሎች የልማት ሥራዎች ሲተገበሩ ማየት ትልቅ ስኬት ነው። በአማራ ክልል አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የቻግኒ ከተማ ነዋሪ አቶ ሲራጅ አዲስ እንዳሉት ግጭት በነበረበት ወቅት በአካባቢው የኢንቨስትመንትና የንግድ እንቅስቃሴ ተዳክሞ ነበር። እሱ ቀርቶ በሰላም ውሎ ለማደር ጊዜው ከባድ ነበር ይላሉ። "የተገኘው ሰላም በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች እና በህብረተሰቡ የጋራ ጥረት በመሆኑ ሰላሙ አስተማማኝና ዘላቂ እንዲሆን ሁላችንም የበኩላችንን መወጣት ይኖርብናል" ብለዋል። አሁን ላይ ያለፈውን የመከራ ጊዜ፣ በሞት የተለየውን ወገን፣ የወደመውን ሀብትና ንብረት በመርሳት በተገኘው ሰላም በጋራ ሰርቶ ራስንና አካባቢውን ለመለወጥ መትጋት እንደሚገባ ነው የመከሩት። ያለፈን በደልና ቅሬታ በእርቅና በይቅርታ በማለፍ ነገን ብሩህ ለማድረግ መትጋት አለብን በማለትም ነው ያስገነዘቡት። አቶ ሲራጅ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት የጉሙዝ ማህበረሰብ ወደ ቻግኒ መጥቶ ያለውን ሽጦ የሚፈልገውንም ገዝቶ ይሄዳል፤ እነሱም ወደ መተከልና ማንዱራ በመሄድ ያላቸውን ይሸጣሉ፤ የፈለጉትንም ገዝተው የሚመጡበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። ይሄን አብሮነት በማጠናከር ሁለንተናዊ የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰላምን ማጽናት ላይ ጠንክሮ መስራት ይገባል። በአማራም ሆነ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ችግር ሲፈጥሩ የነበሩ ወንጀለኞችን አጋልጦ ለህግ ማቅረብ ያስፈልጋል። አሁንም የጥፋት ተልዕኮ ይዘው ችግር ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱትን አደብ እንዲገዙ ማድረግ ተገቢ ነው። ወንጀለኛን ለህግ አጋልጦ መስጠትን ከተለማመድን ነገም አካባቢውን የጦር ቀጣና ለማድረግ የሚፈልጉ የጥፋት ሃይሎች መግቢያ ቀደዳ አይኖራቸውም ይላሉ። ሃገር በአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን በሁሉም ዜጎች የተባበረ ክንድ ትገነባለች፤ ደህንነቷም ድንበሯም ይጠበቃል። ለዛሬው ትውልድ የደረሰችውም የብዙዎች ዋጋ ተከፍሎባት እንደመሆኑ በጋራ በሰላምና በአብሮነት ይሄንኑ ማስቀጠል የግድ ይላል። በተለይም የሰላም ጉዳይ ቅድሚያ ትኩረት የሚወስድ እንደመሆኑ አካበቢን የመጠበቅ የነቃ ተሳትፎን ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ ልታለማውና ልትጠቀምበት የምትችለው ገና ብዙ ያልሰራችበት ሃብት ባለቤት መሆኗ የአንዳንድ ሃይሎችን ቀልብ መሳቡ የሚጠበቅ ነው። ሰላሟ ሲረጋገጥ የዜጎች ደህንነት ሲከበር የተጀመረው የእድገት ጉዞ መፋጠኑ የማይቀር በመሆኑ ሁሉም የድርሻውን መወጣት ይኖርበታል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 111
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 293
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 424
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል።   “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል።   ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 599
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
በብዛት የታዩ
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 2344
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 1153
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
የካራማራ ድል የኢትዮጵያ ጦር በዜያድባሬ ጦር ላይ ታሪካዊ ገድል የፈጸመበት ነው ... በውጊያው የነበሩ የጦር መኮንኖች
Mar 5, 2021 972
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2013(ኢዜአ) የካራማራ ጦርነት ድል የኢትዮጵያ ጦር በሶማሊያ የወራሪው የዜያድባሬ ጦር ላይ ታሪካዊ ገድል የፈጸመበት ነው ሲሉ በአውደ ውጊያው ላይ የነበሩ የጦር መኮንኖች ገለጹ። ኢትዮጵያዊያን ለአገራቸው ሉዓላዊነት ሁልጊዜ ዘብ መቆም አለባቸው ብለዋል።  የካራማራ ጦርነት 43ኛ ዓመት የድል በዓል መታሰቢያ ዛሬ በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኩባ የወዳጅነት አደባባይ ተከብሯል። ሶማሊያን ለ21 ዓመታት ያስተዳደሩት ዚያድባሬ 'ታላቋን የሶማሊያ ሪፐብሊክ ለመመስረት' በሚል "ድንበራችን እስከ አዋሽ ይደርሳል" እያሉ በመዛት የጦርነት ነጋሪት መጎሰማቸው የሚታወስ ነው። ይሄን እውን ለማድረግ በ1969 ግልጽ ወረራ ኢትዮጵያ ላይ ፈጸሙ። የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ.ም የኩባ ወታደሮችም የተሳተፉበት የኢትዮጵያ ጦር የእብሪተኛውን የዚያድባሬ ጦር ካራ ማራ ላይ ድል በማድረጉ የኢትዮጵያ አሸናፊነት በአደባባይ ታወጀ። በካራማራ ጦርነት በአውደ ውጊያው ላይ የነበሩ የቀድሞ የሠራዊት አባላት ብርጋዴል ጀኔራል ሃይለመለኮት ማሞ፣ ሻምበል ባሻ ሁሴን ጎበና እና መቶ አለቃ በቀለ በላይ ድሉን አስመልክቶ የምስክርነት ቃላቸውን ለኢዜአ ሰጥተዋል። ጦርነቱ የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ የገባውን ወራሪውን የሶማሊያ ጦር ከአገር ለማስወጣትና ድል ለማድረግ የሕይወት መስዋዕትነት የተከፈለበት መሆኑንና ኢትዮጵያም በድሉ ክብሯ መጠበቁን ገልጸዋል። በምድርና በአየር ወራሪ የሶማሊያ ጦርን በመደምሰስ የኢትዮጵያ ሠራዊት ታሪካዊ፣ አስደናቂ ገድልና ጀብድ መፈጸሙንም ተናግረዋል። በወቅቱ የነበሩ የሠራዊቱ አባላት ሕይወቴ ከአገሬ አይበልጥም ብለው ያሳዩት ተጋድሎ የማይረሳ ነው ብለዋል የጦር መኮንኖቹ። ኢትዮጵያዊያን ሁልግዜ አገራቸውን ነቅተው መጠበቅ እንዳለባቸውና ለሉዓላዊነቷ ዘብ መቆም እንደሚገባቸው አሳስበዋል። በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደር ቪልማ ቶማስ የካራማራው ጦርነት ኢትዮጵያ በውጭ ወራሪ ኃይል ላይ ያስመዘገበችው ድል መሆኑን ገልጸዋል። በጦርነቱ ላይ የኩባ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ወታደሮች ጎን በመሆን መዋጋታቸውንና 163 ኩባዊያን ወታደሮች የሕይወት መስዋዕትነት መክፈላቸውን ተናግረዋል። "የተገኘው ድል በኢትዮጵያና በኩባ ሕዝቦች መካከል ያለውን የወንድማማችነት ትስስር የሚያሳይ ምስክር ነው" ብለዋል። "ኢትዮጵያና ኩባን ከ43 ዓመት በፊት ያስተሳሰረ የወዳጅነትና ትብብር መንፈስ አሁንም አለ" ያሉት አምባሳደር ቪልማ፤ አገራቱ ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማጠናከር እየሰሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የደቡብ አሜሪካና ካሪቢያን አገሮች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ ቤኩማ መርዳሳ ፣ "የካራማራ ድል ኢትዮጵያዊያን የዚያድ ባሬ ወራሪ ኃይል በኢትዮጵያ ላይ የፈጸመውን ወረራ በመመከት ድል የተጎናጸፉበት ታሪክ ነው" ብለዋል። ድሉ ኢትዮጵያ ወራሪ ሃይልን በማሸነፍ ዳግም ነጻነቷን ያወጀችበትና ኢትዮጵያዊያን የሕይወት መስዋዕትነት ከፍለው ሉዓላዊነታቸውን ያስጠበቁበት እንደሆነም አክለዋል። ኩባ በጦርነቱ ወቅት ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም ያሳየችው አጋርነት ኢትዮጵያ ሁሉጊዜ የምታወሳውና የምትዘክረው እንደሆነም አመልክተዋል። የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አበበ አያሌው ማህበሩ በአጥንትና በደም የተሳሰረውን የኢትዮጵያና ኩባ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን ተናግረው፤ ኩባ ከኢትዮጵያ ጎን ሆና ላሳየችው አጋርነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።  የሰብአዊ መብት ተሟጋች አቶ ታማኝ በየነ "የካራማራ ድል ኢትዮጵያዊያን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ኢትዮጵያን ያቆዩበት ታሪካዊ ገድል ነው" ብለዋል። ኢትዮጵያዊያን በታሪክ ከተገኙ ድሎች በመማር አሁንም ቢሆን ከልዩነታቸው ይልቅ ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም አገራቸውን መጠበቅ እንደሚገባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያዊያን ሁልጊዜም ታሪክ ለሰሩ ወታደሮችና የጦር ሠራዊት አባላት ክብር መስጠት አለባቸው ብለዋል። በኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት አደባባይ በተከበረው የድል በዓል የኩባ አምባሳደር ቪልማ ቶማስን ጨምሮ የተለያዩ አካላት በጦርነቱ ለተሰው ጀግኖች የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። ከኢትዮጵያዊያን የየካቲት ወራት ድሎች አንዱ የሆነው የካራማራ ድል 43ኛ ዓመቱን አስቆጥሮ የድል በዓሉ በኢትዮጵያዊያን ዛሬም እየተከበረ ይገኛል።
ባለፉት ስድስት ወራት በሀገራዊ ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ላይ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ ተሰርቷል--የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Mar 4, 2023 835
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 25 ቀን 2015 በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት በአገራዊ ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ላይ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ መከናወኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተዘጋጀው የፌዴራልና ክልል ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ኢትዮጵያ በጫናዎች ውስጥ ሆናም በተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ተመዝግቧል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት፣ በመልካም አስተዳደር ሥራዎች፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች አበረታች ውጤት ተገኝቷል ብለዋል። ሰላምና መረጋጋትን በማስፈን በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እንደ አገር የተመዘገቡ ስኬቶች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ ለእነዚህ ስኬቶች የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን አስተዋፅኦ ድርሻ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። በመንግስት እና ሕወሓት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት እንዲዝ እንዲሁም በሌሎች አገራዊ ስኬቶች ላይ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ጠንካራ ስራ አከናውኗል ነው ያሉት። "በኢትዮጵያ አክራሪነትና ጽንፈኝነት ውስብስብ ችግሮችን በመፍጠር ተጽእኖ አሳድረዋል" ሲሉ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይሄንን በመመከትም አበረታች ስራ መሰራቱን አመልክተዋል። "የዜጎች ሰላም ወጥቶ በሰላም መመለስ እረፍት የሚነሳቸው የውስጥና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ለማመስ የሚያደርጉትን እኩይ ሙከራ ማክሸፍ ይገባል" ብለዋል። "ኢትዮጵያ የሚያጋጥሟትን ፈተናዎች በድል ተወጥታ የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ እውን እንድታደርግ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በተናበበ አኳኋን መምራት የሚጠበቅብን ወቅት ላይ ደርሰናል" ሲሉ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በዲሞክራሲያዊ ሽግግር ላይ መሆኗን የገለጹት ዶክተር ለገሰ፤ ሂደቱን የተሳለጠ ለማድረግ በዘርፉ የሚከናወኑት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። በቀጣይም አክራሪነትና ፅንፈኝነትን በቅንጅት በመመከት የኢትዮጵያን ሕዝብ የሚመጥን የሚዲያ እና ኮምኒኬሽን ስራ መስራት እንደሚገባም ሚኒስትሩ አሳስበዋል።    
በብዛት የታዩ
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 2344
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 1153
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
የካራማራ ድል የኢትዮጵያ ጦር በዜያድባሬ ጦር ላይ ታሪካዊ ገድል የፈጸመበት ነው ... በውጊያው የነበሩ የጦር መኮንኖች
Mar 5, 2021 972
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2013(ኢዜአ) የካራማራ ጦርነት ድል የኢትዮጵያ ጦር በሶማሊያ የወራሪው የዜያድባሬ ጦር ላይ ታሪካዊ ገድል የፈጸመበት ነው ሲሉ በአውደ ውጊያው ላይ የነበሩ የጦር መኮንኖች ገለጹ። ኢትዮጵያዊያን ለአገራቸው ሉዓላዊነት ሁልጊዜ ዘብ መቆም አለባቸው ብለዋል።  የካራማራ ጦርነት 43ኛ ዓመት የድል በዓል መታሰቢያ ዛሬ በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኩባ የወዳጅነት አደባባይ ተከብሯል። ሶማሊያን ለ21 ዓመታት ያስተዳደሩት ዚያድባሬ 'ታላቋን የሶማሊያ ሪፐብሊክ ለመመስረት' በሚል "ድንበራችን እስከ አዋሽ ይደርሳል" እያሉ በመዛት የጦርነት ነጋሪት መጎሰማቸው የሚታወስ ነው። ይሄን እውን ለማድረግ በ1969 ግልጽ ወረራ ኢትዮጵያ ላይ ፈጸሙ። የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ.ም የኩባ ወታደሮችም የተሳተፉበት የኢትዮጵያ ጦር የእብሪተኛውን የዚያድባሬ ጦር ካራ ማራ ላይ ድል በማድረጉ የኢትዮጵያ አሸናፊነት በአደባባይ ታወጀ። በካራማራ ጦርነት በአውደ ውጊያው ላይ የነበሩ የቀድሞ የሠራዊት አባላት ብርጋዴል ጀኔራል ሃይለመለኮት ማሞ፣ ሻምበል ባሻ ሁሴን ጎበና እና መቶ አለቃ በቀለ በላይ ድሉን አስመልክቶ የምስክርነት ቃላቸውን ለኢዜአ ሰጥተዋል። ጦርነቱ የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ የገባውን ወራሪውን የሶማሊያ ጦር ከአገር ለማስወጣትና ድል ለማድረግ የሕይወት መስዋዕትነት የተከፈለበት መሆኑንና ኢትዮጵያም በድሉ ክብሯ መጠበቁን ገልጸዋል። በምድርና በአየር ወራሪ የሶማሊያ ጦርን በመደምሰስ የኢትዮጵያ ሠራዊት ታሪካዊ፣ አስደናቂ ገድልና ጀብድ መፈጸሙንም ተናግረዋል። በወቅቱ የነበሩ የሠራዊቱ አባላት ሕይወቴ ከአገሬ አይበልጥም ብለው ያሳዩት ተጋድሎ የማይረሳ ነው ብለዋል የጦር መኮንኖቹ። ኢትዮጵያዊያን ሁልግዜ አገራቸውን ነቅተው መጠበቅ እንዳለባቸውና ለሉዓላዊነቷ ዘብ መቆም እንደሚገባቸው አሳስበዋል። በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደር ቪልማ ቶማስ የካራማራው ጦርነት ኢትዮጵያ በውጭ ወራሪ ኃይል ላይ ያስመዘገበችው ድል መሆኑን ገልጸዋል። በጦርነቱ ላይ የኩባ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ወታደሮች ጎን በመሆን መዋጋታቸውንና 163 ኩባዊያን ወታደሮች የሕይወት መስዋዕትነት መክፈላቸውን ተናግረዋል። "የተገኘው ድል በኢትዮጵያና በኩባ ሕዝቦች መካከል ያለውን የወንድማማችነት ትስስር የሚያሳይ ምስክር ነው" ብለዋል። "ኢትዮጵያና ኩባን ከ43 ዓመት በፊት ያስተሳሰረ የወዳጅነትና ትብብር መንፈስ አሁንም አለ" ያሉት አምባሳደር ቪልማ፤ አገራቱ ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማጠናከር እየሰሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የደቡብ አሜሪካና ካሪቢያን አገሮች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ ቤኩማ መርዳሳ ፣ "የካራማራ ድል ኢትዮጵያዊያን የዚያድ ባሬ ወራሪ ኃይል በኢትዮጵያ ላይ የፈጸመውን ወረራ በመመከት ድል የተጎናጸፉበት ታሪክ ነው" ብለዋል። ድሉ ኢትዮጵያ ወራሪ ሃይልን በማሸነፍ ዳግም ነጻነቷን ያወጀችበትና ኢትዮጵያዊያን የሕይወት መስዋዕትነት ከፍለው ሉዓላዊነታቸውን ያስጠበቁበት እንደሆነም አክለዋል። ኩባ በጦርነቱ ወቅት ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም ያሳየችው አጋርነት ኢትዮጵያ ሁሉጊዜ የምታወሳውና የምትዘክረው እንደሆነም አመልክተዋል። የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አበበ አያሌው ማህበሩ በአጥንትና በደም የተሳሰረውን የኢትዮጵያና ኩባ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን ተናግረው፤ ኩባ ከኢትዮጵያ ጎን ሆና ላሳየችው አጋርነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።  የሰብአዊ መብት ተሟጋች አቶ ታማኝ በየነ "የካራማራ ድል ኢትዮጵያዊያን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ኢትዮጵያን ያቆዩበት ታሪካዊ ገድል ነው" ብለዋል። ኢትዮጵያዊያን በታሪክ ከተገኙ ድሎች በመማር አሁንም ቢሆን ከልዩነታቸው ይልቅ ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም አገራቸውን መጠበቅ እንደሚገባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያዊያን ሁልጊዜም ታሪክ ለሰሩ ወታደሮችና የጦር ሠራዊት አባላት ክብር መስጠት አለባቸው ብለዋል። በኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት አደባባይ በተከበረው የድል በዓል የኩባ አምባሳደር ቪልማ ቶማስን ጨምሮ የተለያዩ አካላት በጦርነቱ ለተሰው ጀግኖች የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። ከኢትዮጵያዊያን የየካቲት ወራት ድሎች አንዱ የሆነው የካራማራ ድል 43ኛ ዓመቱን አስቆጥሮ የድል በዓሉ በኢትዮጵያዊያን ዛሬም እየተከበረ ይገኛል።
ባለፉት ስድስት ወራት በሀገራዊ ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ላይ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ ተሰርቷል--የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Mar 4, 2023 835
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 25 ቀን 2015 በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት በአገራዊ ዕድገትና ገጽታ ግንባታ ላይ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ መከናወኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተዘጋጀው የፌዴራልና ክልል ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ኢትዮጵያ በጫናዎች ውስጥ ሆናም በተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ተመዝግቧል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት፣ በመልካም አስተዳደር ሥራዎች፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች አበረታች ውጤት ተገኝቷል ብለዋል። ሰላምና መረጋጋትን በማስፈን በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እንደ አገር የተመዘገቡ ስኬቶች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ ለእነዚህ ስኬቶች የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን አስተዋፅኦ ድርሻ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። በመንግስት እና ሕወሓት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት እንዲዝ እንዲሁም በሌሎች አገራዊ ስኬቶች ላይ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ጠንካራ ስራ አከናውኗል ነው ያሉት። "በኢትዮጵያ አክራሪነትና ጽንፈኝነት ውስብስብ ችግሮችን በመፍጠር ተጽእኖ አሳድረዋል" ሲሉ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይሄንን በመመከትም አበረታች ስራ መሰራቱን አመልክተዋል። "የዜጎች ሰላም ወጥቶ በሰላም መመለስ እረፍት የሚነሳቸው የውስጥና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ለማመስ የሚያደርጉትን እኩይ ሙከራ ማክሸፍ ይገባል" ብለዋል። "ኢትዮጵያ የሚያጋጥሟትን ፈተናዎች በድል ተወጥታ የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ እውን እንድታደርግ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በተናበበ አኳኋን መምራት የሚጠበቅብን ወቅት ላይ ደርሰናል" ሲሉ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በዲሞክራሲያዊ ሽግግር ላይ መሆኗን የገለጹት ዶክተር ለገሰ፤ ሂደቱን የተሳለጠ ለማድረግ በዘርፉ የሚከናወኑት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። በቀጣይም አክራሪነትና ፅንፈኝነትን በቅንጅት በመመከት የኢትዮጵያን ሕዝብ የሚመጥን የሚዲያ እና ኮምኒኬሽን ስራ መስራት እንደሚገባም ሚኒስትሩ አሳስበዋል።    
የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂና በስትራቴጂ የታገዘ ስራ እየተከናወነ ነው -ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ
Mar 3, 2023 772
ባህር ዳር (ኢዜአ) የካቲት 24/2015 የግብርናው ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂና በስትራቴጂ የታገዘ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለ አስታወቁ። የክልሉ ግብርና ቢሮ ዛሬ 241 የእርሻ ትራክተሮችን ለአርሶ አደሮች አስረክቧል። ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ በወቅቱ እንደገለጹት ባለፉት አመታት ለግብርናው ዘርፍ ትኩረት የተሰጠ ቢሆንም አሰራሩ የአርሶ አደሩን ምርታማነት በማሳደግ በኩል ለውጥ ሳይመጣ ቆይቷል። የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂና በስትራቴጂ የታገዘ ስራ እየተከናወነ ነው። ከቅርብ አመታት ወዲህ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት በተግባር የታገዘ ለውጥ የሚያመጣ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በስንዴና አኩሪ አተር ምርት በክልሉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል። የክልሉ መንግስት የአርሶ አደሩን ጊዜ የሚቆጥቡና የምርት ብክነትን የሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎችን በረጅም ጊዜ የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። አርሶ አደሩን በቴክኖሎጂ የማዘመንና በረጅም ጊዜ ክፍያ የቴክኖሎጂ ግብዓቶች እንዲያገኝ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። በግብርናው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት በተለመደው መንገድ መሄድ እንደማያዋጣ የገለጹት ደግሞ የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ ናቸው። የግብርና ምርታማነትን በፍጥነት ለማሳደግ ዘመኑ ያፈራቸውን ጊዜ ቆጣቢና የአርሶ አደሩን ድካም የሚቀንሱ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል። ባለፉት ዓመታት መንግስት የግብርናውን ዘርፍ የሚያዘምኑ ውሳኔዎችን በማስተላለፍ የእርሻ ቴክኖሎጂዎች ከቀረጥ ነጻ እያስገባ መሆኑን ተናግረዋል። በሃገር አቀፍ ደረጃ ቴክኖሎጂን ተጠቅሞ ምርታማነትን በማሳደግ በኩል ብዙ እንደሚቀር የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ከሚታረሰው መሬት 22 በመቶው ብቻ በትራክተር እየታረሰ መሆኑን ገልጸዋል። አርሶ አደሩ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆን አስቻይ ሁኔታዎች መቅደም እንዳለባቸው አመልክተው፤ ለዚህም አንዱና ዋነኛው መሬትን በኩታ ገጠም ማረስ እንደሆነ አብራርተዋል። ለዚህም ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆናቸውን የተናገሩት ዶክተር ግርማ፤ አሁን ላይ እንደ ሀገር 6 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም ተደራጅቷል ብለዋል። ''አርሶ አደሩ በቴክኖሎጂ ተደራሽ እንዲሆን በማድረግ ምርታማነትን ለማሳደግ ሰፊ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው'' ያሉት ደግሞ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኃይለማሪያም ከፍያለው ናቸው። በክልሉ ለዓመታት የነበሩት ትራክተሮች ከ800 ያልበለጡ እንደነበሩ አስታውሰው፣ ባለፉት ሁለት ዙሮች ብቻ ከ700 በላይ ትራክተሮች ለአርሶ አደሮች ማስረከብ ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ በዘር በመሸፈን ላይ ከሚገኘው 4 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር የእርሻ መሬት 11 በመቶው ብቻ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሚታረስ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም ለአርሶ አደሮች ትራክተሮችን የማቅረብና ሌሎች የማዘመን ጅምር ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። የክልሉ መንግስት በረጅም ጊዜ ክፍያ የትራክተር ባለቤት እንዲሆኑ ማድረጉ እንዳስደሰታቸው የገለጹት ደግሞ ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን ደንብያ ወረዳ የመጡት አርሶ አደር አሰፋ አያሌው ናቸው። አርሶ አደሮቹ የተረከቧቸው የእርሻ ትራክተሮች የተለያየ የፈረስ ጉልበት እንዳላቸው ተገልጿል። በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የክልሉና የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም አርሶ አደሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት ከብልሹ አሰራርና ሌብነት ጋር በተያያዘ ከ200 በላይ አመራርና ሰራተኞች ላይ ክስ ተመስርቷል"-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Feb 26, 2023 771
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 ባለፉት ስድስት ወራት ከብልሹ አሰራርና ሌብነት ጋር በተያያዘ ከ200 በላይ አመራርና ሰራተኞች ላይ ክስ መመስረቱን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ዛሬ ተጠናቋል። በማጠቃለያው ወቅት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ብልሹ አሰራርና ሌብነትን የመከላከል ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አገልግሎት አሰጣጥን ከወቅቱ ጋር እንዲሄድ ለማስቻል በርካታ ዘርፎችን የማዘመን እና የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት ጫናን በመቀነስ የነዋሪውን ችግር እንዲያቀሉ የተጀመሩት የእሁድ ገበያ እና የሌማት ትሩፋት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ጠቁመዋል። በእሁድ ገበያ ለመሰረታዊ ፍጆታ የሚሆኑ ምርቶች በቀላሉ ህብረተሰቡ ጋር እንዲደርሱ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል። አስተዳደሩ ከተማዋን ለነዋሪዎች ጽዱ፣ ውብና ምቹ ከማድረግ ባሻገር ዓለም አቀፍ የዲፕሎማቲክ ከተማነቷን የምትመጥን ለማድረግ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ ተግባራዊ እያደረገ ነውም ብለዋል። “ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከር አመራራችን ፅንፈኝነትን፣ ጥላቻን፣ የህብረተሰቡን አንድነት የሚንዱ አስተሳሰቦችን፣ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚደረጉ የሚዲያ ዘመቻዎችንና ሌሎች የፓርቲያችን እሳቤ ያልሆኑ አመለካከቶችን በመዋጋት ረገድ እየተሰራ መሁኑ ተናግረዋል። “አሁንም ወደ ከተማ የሚደረገው ፍልሰት እና በህቡእ አደረጃጀት የሚደረግ ህገ-ወጥነት ላይ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል” ሲሉ መግለጻቸውን ከንቲባ ጽህፈት ቤት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያሰፈረው መረጃ ያመለክታል። በቀሪ የበጀት አመቱ ወራት ያልተከናወኑ ተግባራት ተለይተው በእቅድ ክለሳ እንዲካተቱ በማድረግ የህዝቡን ኑሮ የሚያቀሉ ፕሮጀክቶች ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት እንደሚሰሩም ከንቲባ አዳነች አክለው ገልጸዋል።
ሴትነት እና እናትነት
Mar 8, 2023 743
(አየለ ያረጋል) እስኪ መላ ስጪኝ መላ ካንቺ ይገኛል እኔማ ወንድ ነኝ ይደናገረኛል… (የማኅበረሰቡ ቃላዊ ግጥም) ሴትነት እናትነትን ለመግለጽ ቀርቶ በጥቂቱ ለመረዳት የ’እናት ልብ’ መታደል የሚሻ ይመስላል። ጥቂት ወንዶች ይህን ጸጋ ይቸራሉ። ልክ እንደ ዶክተር ይሁኔ አየለ። የስነ-ምግብ ሳይንቲስቱ ዶክተር ይሁኔ አየለ ‘እናት’ በሚል ርዕስ ባሳተሙት ድንቅ መጽሐፍ የሴትነት እና እናትነትን ከፍታ በ’ኩርሽም’ ቃላት ተራቀውበታል። የሴቶች ቀንን (ማርች-8) ሰበብ በማድረግ ይህን ጽሑፍ ሳዘጋጅ መታሰቢያነቱ እናትን አስበው በ‘እናትነት’ ቅን ልቦና ‘እናትን’ ላበረከቱልን ዶክተር ይሁኔ አየለ ነው። ‘እናት፤ የሴት ልጅ ስንክሳር፤ ከቤተሰባዊ ሕይወት እስከ ሐልዮመንበርት’ በሚል ርዕስ በቅርቡ ባሳተሙት (በ406 ገፆች በተቀነበበ) አርበ ጠባብ መጽሐፍ ሴትነትን ከዘፍጥረት እስከ አሁን ዘመናትን ዋጅተው፣ እናትነትን ከሴትነት ዘንቀው፣ የእናትነት ጸጋን ከነባራዊ ሃቅ ጋር አሰነናስለው፣ የእናትነትን ልዕለ-ተፈጥሮ አርቅቀው፣ የዓለምን ክብር-ነሽነት ከነገረ-ሃይማኖት እስከ ነገረ-ባህልና ፍልስፍና ፈትተው፣ የማኅበረሰቡን ምልከታ ዝንፈት እና ሚዛን ጉድለት ከማኅበራዊ እስከ ፖለቲካዊ መገለጫዎች አዛምደው አቅርበውታል። ዶክተር ይሁኔ አየለ “እናት” በተሰኘ እናት የሆነ መጽሐፋቸው እናትነትን በልኩ ነጽረውታል። ሴትነት በኢትዮጵያ የአስተሳሰብ ሰለባነቱን፣ ነገረ-ሴትነትን ከንጽረተ-ሴትነት ቃኝተውታል። በእሳቤ ሚዛን ሰለባነት ዓለም ውስጥ ከንግስት ማክዳ እስከ ንግስት ፉራ፣ ከሰብለ ወንጌል እስከ ድል ወንበራ፣ … ብርቱ ኢትዮጵያዊት ሴቶችን ሕይወት ጨልፈውታል። የሴትነትን ጸጋዎች ጨልፈው በሴትነት ላይ የሚፈጸሙ የሀበሻ ግፎችን ተንትነውበታል። ሴቶች የማኅበረሰቡ ግፍ ሰለባዎች፣ የማኅበራዊ ፍትህ ጉድለት ሰለባዎች እንደሆኑ በቅጡ ገልጸውታል። ዳሩ ሴትነት ጀግና እና ብልህ፣ የቤተሰብ መሰረት፣ የደስታና እልልታ እናት፣ ቃል ኪዳንና ክብር ጠባቂ እንደሆነ ገልጸዋል። “ሴት ልጅ ባለብዙ ጸጋዎች ናት። ከጸጋዎቿ መካከል ጀግንነት እና ብልሃት ይጠቀሳሉ። … ሴት ልጅ ባህልን ፈጥራ የማኅበራዊነትን ማስተሳሰሪያ ገመዶች ገምዳ አስተሳስራ ማኅበረሰብን የተከለች ሥርዓት ናት። … ቤተሰብ የአንድ ማኅበረሰብ የመጀመሪያ ተቋም ነው። የተቋሙ ባለሥልጣን (እመቤት) ሴት ናት። ያቺ ሴት እናት ናት። ቤተሰብ የስብዕና መሰረት የሚባለው እናትን ምሰሶ አድርጎ ነው” (ገጽ-285) ሴት ልጅ መለኛ መሆኗን ማኅበረሰባችን ቢያምንም ሴትነትን ግን እንዳላከበረ አሉታዊ ይትባህልና ኪነተ- ቃሉን ዘይቤ ያወሳሉ። በእርግጥ የእናትን ምቹነት እና ዋጋ ከፋይነት የሚያትቱ የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎችም አሉ። ለምሳሌ ዳንኤል አበራ “የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎች” በሚለው መጽሐፋቸው “እናት ትረገጣለች እንደመሬት፤ እናት ለልጄ ልጅ ለነገዬ፤ እናቷን አይተህ ልጅቷን አግባ፤ እናት የሌለው ልጅ እንደ ጌሾ፤ ሳይበላ የበላ ሳይናገር ዋሾ…” የሚሉ ምሳሌያዊ ንግግሮችን አስፍረዋል። መላኩ ይርዳው የተባሉ ጸሐፊ ‘ደቦ ቅጽ-፩’ ከተሰኘው የ60 ደራሲያን ሥራዎችን ያካተተ መጽሐፍ ውስጥ ‘የሴትነት ጸጋ’ በሚል በጻፉት መጣጥፍ ሴትነትን ከፍቅር፣ ከጥበብ፣ ከብልሃትና ልዕልና ጋር አቆራኝተውታል። “ሴት ልጅ ቅኔ ናት፤ ከተባለላት፣ ከተጻፈላት፣ ከተዜመላት በላይ የረቀቀች ረቂቅ ቅኔ ናት። እስከዛሬ ከያኒያን ስለሴት ከተራቀቁት፣ ከተጠበቡት ሁሉ እኔ ለማውቃት ሴት ሁሉ የሚመጥኑ ሆነው አልታዩኝም። የሴትነት ጸጋው ብዙ ነውና የሴትን ትክክለኛ ማንነት መርምረን አጥንተን የደረስንበት ውስጠ-ስሪቷን አጥንተን የተረዳነው አይመስለኝም።… ከታላቅነቷ፣ ከብልሃቷ፣ ከረቂቅነቷ፣ ከመግዛት አቅሟ፣ ከርህራሄዋ፣ ከሰላማዊነቷ ከሌሎችም አያሌ በረከቶች አንጻር ለሴት ልጅ የተደረገላት፣ የተነገረላትና የሆነላት ሁሉ ያንስብኛል” ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) ስለሴት ልጅ ጭቆና የታገለ እና ስለክብሯ የዘመረ ምሁር ነው። ስለሴት ልጅ ስቃይና ሰቆቃ አትቷል። ‘በናቴኮ ሴት ነኝ’ በሚለው መጽሐፉ ስንኞች እንምዘዝ! …. ግማሽ አካሏ ወንድ በትምክህት ቢከዳት ጧ! ብላ አለቀሰች አዛኝ ቢደርስላት፣ … ብሶት ተጫጭኗት ምንም ሰው አልሆነች በቀቢጸ ተስፋ ሕላዌንም ጠላች ያገሬ ጭቁን ሴት መድኅን መላ ያጣች….! ‘ሔዋንያት የትውልድ ፋብሪካዎች ናቸው፤ እነሱ ባይኖሩ ዓለም ባዶ ትሆን ነበር’ እንዲል ፈላስፋው ሶቅራጥስ። ስለሴት (ግማደ ሰቧ ፍጡር) ግፍና በደል ገሞራው እንዲህ ይላል። “መራራ ጭቆና በሰፈነበት ምዝብር ሕብረተሰብ ውስጥ ታፍነው የሚኖሩ ሔዋንያት ብሶታቸው፣ ፍዳቸው፣ በደላቸው፣ ጭንቀታቸውና መከራቸው እንደ ሰማዕታት ገድል እጥፍ ድርብ ነው…. አጉል ልማድ፣ ኋላቀር ባሕልና አድሃሪ ሕገ-ማኅበረሰብ ከከንቱ አስተሳሰቦች ጋር ተዳምሮ በአንድነት በመመሳጠር ዘርዓ ሔዋንን ሲጫወቱባቸው ሲያሾፉባቸው ኑረዋል” (ገጽ-23) በሥነ-ሕይወት ሳይንስና በትምህርተ-ጄነቲክስ (አካለ ሕላዌ) ሴቶችን ከወንዶች የሚያሳንስ ምንም አይነት አካላዊ ተሰጥኦ እንደሌለ ተረጋግጧል። ታሪክና ተረክ ግን ወገንተኛ መሆኑን ገሞራው ይናገራል። ተረክና ተረት አልባሌ ታሪክ የሚፈጥሯቸው አርበኞች ሁሉ በፆታቸው ተባዕት በመሆናቸው፤ በሴቶች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ በማሳደሩ ሊኖራቸው የሚችለው ዕድገት ላይ ትልቅ ደንቃራ ሆኖ መቆየቱን ይገልጻል። “የታሪክን ሁኔታዎችን የመመንዘር ትርጓሜያዊ አንጻር የታሪክን ትዕይንቶች ብንመረምር አንደርድሮ የሚያደርሰን ሴቶች ከወንዶች የከፋ ባህሪያዊ ድክመት እንዳለባቸው ከሚያሳይ ሥዕል ላይ ነው።” በሚት(ተለጣጭ ተረክ) ላይ የሚራቀቁት አቶ ቴዎድሮስ ገብሬ (በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፎክለር መምህር) ‘ተረኮች እማዊ ሳይሆን አባዊ ናቸው’ በማለት ይህን ጉዳይ ያጠናክሩታል። “በሚት ውስጥ ገነው ከሚታዩ አበይት ማኅበራዊና ባህላዊ እውነታዎች መሃል አንዱ ፆታዊ ወገንተኝነት ነው። የሰማናቸው፣ ያነበብናቸው ሚታዊ ተረኮች በእጅጉ አባዊ ለሆኑ ሥርዓቶች (ፓትሪያርካል ሲስተምስ) ያደሩ፣ በአብዛኛው በተባዕት ተጋዳሊያን የተሞሉ ናቸው” ይላል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዶክተር ይሁኔ (በገፅ-401) ስለሰው ማንነት ቀረጻ በተመለከተ ከጥንት እስከ ዛሬ አከራካሪ የሆኑ ፈላስፎችን ክርክር ያነሳሉ። ይኸውም የሰው ልጅ ‘ማን ቀረጸኝ? ተፈጥሮ ወይስ ተሞክሮ?’ የሚለውን መከራከሪያ ጽንሰ-ሃሳብ ይፈትሻሉ። በዚህም “ሰዎች ሲፈጠሩ የሰውየውን ችሎታ ይዘው ነው” እና “የሰዎች ማንነት የሚቀረጸው ከውልደት በኋላ በተሞክሮ ወይም ከአካባቢ ጋር በሚኖራቸው መስተጋብር ነው” የሚሉትን ሃሳቦች ወስደው ከእናት ሚና ጋር ያዛምዱታል። እናም እናት ‘በየትኛውም መደብ ልጅን አሳምራ ትቀርጻለች’ የሚል ድምዳሜ ሰጥተዋል። “በየትኛውም መንገድ በሰው ልጅ ላይ የእናት ቀራፂነት ስለሚኖር ከተጽዕኖዋ ማምለጥ የሚቻል አይመስለኝም።… አካባቢም ሰውን ይሰራዋል የሚሉትም ከውልደት በፊትም ሆነ በኋላ ከተፈጥሮ ጋር የሚደረገው ውስብስብ መስተጋብር ‘ሰው’ በመሆን ላይ ጉልህ ሚና ይጫወታል” ይላሉ። በዚህ እሳቤ ሰው የወላጆቹም፤ የአካባቢውም ውጤት መሆኑን በግልጽ እንረዳለን” ይላሉ። ሴቶች ከጥንት እስከ ዛሬ በኢትዮጵያ ማኅበረ-ባህላዊ እንዲሁም ለሰላምና ዕርቅ እሴቶች ጉልህ ሚና አላቸው። ሴቶች ያልተሳተፉበት ዘርፍ የለም። ከመሪነት፣ ጥበበኝነት፣ ከአገር ድንበር ጠባቂነትና የዲፕሎማሲያዊ ሚና… መጥቀስ ይቻላል። ሴቶች በሁሉም ማኅበረሰብ ዘንድ በሰላምና ግጭት አፈታት ግንባር ቀደም ተሰሚነት አላቸው። ለአብነትም ሀደ ሲንቄ፣ በሶማሌ-ሔር፣ በሲዳማ-ያካ፣ በራያ ማኅበረሰብ ዱበርቲዎች፣ በስልጤ-ሴረን ባህል መጥቀስ ይቻላል። ከሰሞኑ ባከበርነው የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ሴቶች ውለታ በወፍ በረር ማውሳት ይቻላል። የኢትዮጵያ ሴቶች ከሌላው ዓለም ሴቶች በተለየ የራሳቸው ቀለም ያላቸው፣ የአመራር ልምድ ያዳበሩ፣ የመወዳደሪያ ስነ-ልቦና ያላቸው፣ ችለው አሸንፈው ያሳዩ ናቸው። ሴቶች ድሉን በማስመዝገብ የተጫወቱትን ሚና ያህል፣ ገድላቸው በታሪክ በሚገባ አልተወሳም። ዶክተር አልማው ክፍሌ የተባሉ የታሪክ ምሁር በአንድ ወቅት ሚዲያ ላይ ቀርበው “በአድዋ ጦርነት ዘማቾች 75 በመቶ ሴቶች ነበሩ” ሲሉ ሰምቻለሁ። በአድዋ ጦርነት ሴቶች በተለያዩ ሙያዎች ተመድበው ከካምፕ እስከ ጦር ሜዳ ከመመገብ እስከ ማጀገን፣ ከማከም እስከ መዋጋት ድንቅ ሚና ተወጥተዋል። ድርብ ድርብርብ ኃላፊነት ይዘው የዘመቱ፣ ለወንዶችም ልብ፣ ሞራልና ወኔ አቀባዮች ነበሩ። እቴጌ ጣይቱን መሰል የአድዋ ሴት የጦር ፊታውራሪዎች በርካታ ናቸው። ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ ወልደአረጋይ ‘ታሪክ ዘመን ዘዳግማዊ ምኒልክ’ በተሰኘው መጽሐፋቸው የሴቶችን ሚና በተመለከተ እንዲህ ይላሉ፡- “እንዲህም እየሆነ፣ አጤ ምኒልክ ባዳራሹ እቴጌ ጣይቱ በእልፍኝ ባለሟሎችዎን ወይዛዝርቱን ይዘው ግብሩ አንድ ቀን ሳይጎድል፣ ይዘምታሉ። ከዘመቻ ላይ ጠጁ ማሩ አለመጉደሉ፣ ስለምንድነው ያልህ እንደሆነ ይህን ታሪክ መመልከት ነው። በስድስት ድንኳን እንጀራው ሲጋገር ሲያድር፣ በአራት ድንኳን ወጡ ሲሠራ ሲያድር፣ ጠጁ በቀንድ በኮዳ ደግሞ ሦስት መቶ ስድስት መቶ የሚሆን ገንቦኛ ሲጓዝ ግብሩ ይጎድል ይመስልሀል” (ገጽ-241) ደራሲ በዕውቀቱ ሥዩም ‘ከአሜን ባሻገር’ በተሰኘ መጽሐፉ ‘ሴቶች በዋሉበት’ በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ሴቶች ተጋድሎና ሚና “ከቁስ ባሻገር ከልብ ያቀርባሉ” ይላቸዋል። “ሴቶች ባዋላጅነት ከነበራቸው የማይተናነስ ሚና በጦር ሜዳ ተጫውተዋል። እናቶቻችን በጦር ወቅት፣ መሳሪያ ያቀርቡ ነበር። ምግብ ያቀርቡ ነበር። ሃሳብ ያቀርቡ ነበር። ልብ ያቀርቡ ነበር። ደስታ ያቀርቡ ነበር። ኧረ ምኑ ቅጡ። ሴቶች ባንድ በሙቀጫ ዙሪያ፣ ማኅበረሰቡን ኬሚስት፣ ገጣሚና የፖለቲካ ተንታኝ ሆነው ማገልገላቸውን ልብ እንበል” ይላል። (ገጽ-138) ዶክተር ይሁኔ (በገጽ-14) በበኩላቸው እናቶችን ሩህሩሆች፣ አጉራሽና አልባሽ፣ የችግር ቤዛዎች፣ ሕይወት ዑደት አስቀጣዮች፣ የሕይወት መድኅኖች፣ ባለብዙ ጸጋዎች፣ መልካም ባህሪ አውራሾች፣… በማለት ገልጸውታል። መላ ሴቶችንም በእናቶች አተያይ ማየት እንደሚገባም እንዲሁ። “እናትነት መልካም ገጽታዎችን ደራርቦ የያዘ የሴት ልጅ ትልቅ መገለጫ ነው። እናትነት ከፍ ያለ ሥልጣን ነው። እናትነት ጥልቅና ሰናይ ባህሪያት የሚፈልቁበት ምንጭ ነው። እናትነት የደግነት፣ የጥራት፣ የልህቀትና ተፈላጊነት ማሳያ ተምሳሌት ነው። እናትነት ሞት የማያደበዝዘው ኃያል መንፈስ ነው። እናትነት ከባድ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነው። … እናትነት የሰላም፣ የመልካም ግንኙነትና እንክብካቤ መፍለቂያ አድባር ናት። እናትነት ሰፊና ጥልቅ የሕይወት ትምህርት ቤት ነው። እናትነት ሌሎች ከስቃይ ነፃ እንዲሆኑ፣ ምቾት እንዲሰማቸው በሚደረግ ትግል ውስጥ ዋጋ እየከፈሉ መኖር ነው” በመቀጠልም የኢትዮጵያ እናቶችን ‘ጠቃሚ ነገር ሰጪዎች’ ይላቸዋል። “እናቶች ሰው የመሆኛ ቅመሞች የሚጨለፍባቸው ባህር ናቸው። … ሕይወታዊ ስሪታችን ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን የወሰደው ከእናት ነው። ከእናት የምናገኘው ‘ማይቶኮንድሪያ’ (ማይቶኮንድሪያ የኃይል ማመንጫ ክፍል ሲሆን የምንመገበው ምግብ እየተቃጠለና ወደ አስፈላጊው ኃይል እየተቀየረ ሕይወትን ያንቀሳቅሳል) የምግብ ማቃጠያ ምድጃ ወይም ኃይል ማመንጫ ቤት ሆኖ ያገለግላል። … ብዙ መልካም ስብዕና መገለጫዎች ምንጫቸው የእናት ፍቅር፣ የመልካም ስብዕና እና የርህራሄ ምንጭ ነው” (ገጽ- 61) ኢያሱ በካፋ ‘የኢያሱ በካፋ ወጎች’ በተሰኘው መጽሐፉ እናትነትን ማህጸንን፣ ምግብን፣ ትንፋሽን፣ ደም፣ ሥጋን እና ነፍስን ሰጥተው በረቂቅ ተፈጥሮ ሰውን ከመውለድ ባለፈ ፍቅራቸውን ዘላለማዊ ገደብ አልባ እና ዕልቆ-ቢስ እንደሆነ እንዲህ ገልጾታል። “እናትነት ነፍስን ማካፈል ነው፤ እናትነት የማይደበዝዝ ዘላለማዊ ፍቅር መስጠት ነው፤ እናትነት ከራስ ሕልውና ይበልጥ ለልጅ ማሰብ ነው፤ እናትነት ፍፁም ወረት አልባ መሆን ነው። እናት ለልጇ ያላት ፍቅር አይነጥፍም፤ አይለወጥም። ለእናት ልጇ ሁሌም ልጇ ነው” (ገጽ-4) እናትነት በቃላት ለመግለጽ እንደሚከብድ፤ በውለታ ማካካስ ይከብዳል። የእናት ውለታዋን መክፈል የሚችል ልጅ የለም። የእናት ፍቅርን ለመግለጽም በርካቶች አንደበታቸው ይተሳሰራል፤ ቃላት ይነጥፍባቸዋል፤ ስሜታቸውን መግራት ይሳናቸዋል። ድምፃዊ እሱባለው ይታየው(የሺ) ‘ይናገራል ፎቶ’ በሚል እናትና አባቱን በገለጸበት ሙዚቃ የመጨረሻው ማጠንጠኛው ‘እወድሻለሁ/እወድሃለሁ’ ያለው፤ እንዲሁም ድምፃዊት ብዙነሽ በቀለ ‘እናት ውለታዋ’ በተሰኘ ዘፈኗ ውስጥ (ዜማና ግጥም ጋዜጠኛ ሰለሞን ተሰማ)፤ “ወላጅ እናት እኮ ፍፁም በመንፈሷ፣ ልጇን ትወዳለች አብልጣ ከራሷ” እያለች በሚስረቀረቅ ድምጿ የምታንጎራጉረው ለዚህ ይመስላል። ዕውቁ የቋንቋ ሊቅ የሻው ተሰማ (የኮተቤው) ‘የጥቁር አፈር ትሩፋቶች’ በተሰኘው መጽሐፉ (ገጽ-79) ‘መቀነትሽን አጥብቂ’ በሚል ርዕስ ባሰፈረው ረዘም ያለ ግጥም ሁለት አንጓዎች ብቻ ስንመዝ የእናትነት ውለታን መመለስ እንደሚሳን፤ የእናትነት ግብሯ ‘እናት’ የሚለው ቃል በራሱ እንደሚያንስባት ያትታል። … “ለዚህ ወሮታሽ አጸፋ፤ እናት ይልሻል አገሩ፤ እኔም እናቴ ብልሽ መች ሊመጥንሽ ዳሩ። … እናትነት ምጡቅ ነው፤ እናት ከመባል ይልቃል፤ የግብርሽ ስንክሳር ዚቁ፤ በስያሜ መች ያልቃል”… በማለት ይገልጸዋል። መውጫ ዶክተር ይሁኔ የሴት እና እናትን የነገዋን መንገድ ከሳይንስ አተያይ አንጽረው፤ ከማኅበረ-ፖለቲካ፤ ከማኅበረ-ባህል ከፍታዋ አመሳክረው፤ እናትና ሀገርን መጋመድ አመስጥረው መልእክታቸውን እንደ መውጫ አስፍረዋል። ለስንበት አንድ አንቀጽ እንወርውር!! “የእናት ሀገር ህልውና ከእናቶች ሕይወት ጋር በቀጥተኛ ተዛምዶ አለው። የሰመረ ትውልድ ሊቀጠል የሚችለው በጥሩ ሁኔታ በተገነባ የእናቶች አቅም ነው። የእናቶች አቅም ሲገነባ የራሳቸውን አቅም ያውቃሉ፤ ምርጫቸውን በራሳቸው ይወስናሉ፤ እንዲሁም ለሚመጣው ማኅበራዊ ለውጥ የራሳቸውን አሻራ ያሳርፋሉ። ስለሆነም የእናቶችን አቅም ማጎልበት ትውልድን ማጎልበት ነው። እናቶች ላይ መሥራት ትውልድ ላይ መሥራት ነው”  
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በፈረንሳይኛና ትግሪኛ ቋንቋዎች መረጃዎችን ተደራሽ የሚያድረግ ድረ-ገጽ አስጀመረ
Mar 4, 2023 713
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 25/2015፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ መረጃዎችን በፈረንሳይኛና ትግሪኛ ቋንቋዎች ተደራሽ የሚያደርግ አዲስ ድረ-ገጽ አስጀመረ። አዲሱን ድረ-ገጽ በይፋ ስራ ያስጀመሩት የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ትዕግስት ሀሚድ ናቸው። የተቋሙ ዌብ አድሚኒስትሬተር ሄኖክ አብይ በማስጀመሪያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት አዲሱ ድረ-ገጽ መረጃዎችን በተለያዩ ቋንቋዎች በእኩል ጥራት ለማድረስ የሚያስችል ሆኖ የተገነባ ነው።   የተቋሙን ብራንድ መሰረት ባደረገ መልኩ የተዘጋጀው ድረ-ገጹ ከመረጃ ጥራትና ደኅንነት አንጻርም አስተማማኝ ሆኖ አገልግሎት እንዲሰጥ በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አማካኝነት መገንባቱንም ገልጸዋል። ድረ-ገጹ ከዚህ ቀደሞ በተቋሙ ሲሰራባቸው የነበሩትን እንግሊዝኛ ፣ አረብኛ ፣ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞን ጨምሮ በአዲስ መልኩ በቅርቡ የተጀመሩትን ፈረንሳይኛና ትግሪኛ ቋንቋዎችን በማካተት አገልግሎት እንዲሰጥ ሆኖ መደራጀቱን አስታውቀዋል። የኢዜአ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ እንዳሉት ኢዜአ የኢትዮጵያን ገጽታ የሚገነቡ ሀገራዊ ጉዳዮችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ተደራሽ የሚያደርጉ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ። አሁን ይፋ የሆነው አዲስ የድረ-ገጽ ይሀንኑ አላማ ለማስፈጸም የሚያግዝ ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚው አስተማማኝነቱና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆኖ ዘመናዊ አገልግሎት ማቅረብ እንዲያስችል በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር መገንባቱን ተናግረዋል። በቀጣይም ኢዜአ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዘርፉ ልማት ዙሪያ የሚያከናውናቸውን ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ትዕግስት ሀሚድ በበኩላቸው ተቋማቸው የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ከኢዜአ ጋርም በዘርፉ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን ለመከላከል በጋራ ከመስራት ባለፈ በቀጣይም በዚህና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ግንኙነት የሚያሳድጉ ተግባራትን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። በድረ-ገጹ የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።  
መጣጥፍ
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 557
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ)
Jan 25, 2023 596
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ) አየለ ያረጋል (ኢዜአ) መዳረሻዬ ሽሬ እንዳስላሴ ነው። ለዘገባ ሥራ ከባህርዳር- ጎንደር- ደባርቅ- ሸሬ መንገድ ከሚዲያ ባልደረቦች ጋር እየተጓዝኩ ነው። የጥምቀት ሙሽራዋ ጎንደር እየተኳኳለች ነበር። ደባርቅ ከመድረሴ በፊት ዳባት ትገኛለች-የደጃች አያሌው ብሩ ቁርቁር ከተማ። ደጃች አያሌው ትውልዳቸው በጌምድር ጋይንት ቢሆንም ግዛታቸውና ኑሯቸው ዳባት ነበር። ሞገደኛው ደጃዝማች አያሌው ብሩ በጎንደር ማኅበረሰብ ዘንድ ዝናቸው የናኘ ነው። ደጃዝማች አያሌው በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ (ከልጅ ኢያሱ እስከ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ-መንግሥት) ታሪካዊ ክንውኖች ጉልህ ተሳትፎ አላቸው። አንዷን ብቻ ልምዘዝ። ራስ ተፈሪ ‘ንጉሠ-ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ’ ደጃች አያሌው የቅርብ ዘመዳቸውን ራስ ጉግሳ ወሌ ብጡልን (የንግሥት ዘውዲቱን ባለቤት) ወግተው የጎንደር ግዛት ‘ራስ’ ተብለው ለመሾም ቃል ቢገባላቸውም፤ ተልዕኳቸውን ተወጥተው ቃሉ ባለመፈጸሙ ደጃዝማቹ ከአጼው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። በዚህም:- "አያሌው ሞኙ፣ ሰው አማኙ ሰው አማኙ፣ የአያል ጠመንጃ፣ ስሟን እንጃ ስሟን እንጃ…” በማለት የጎንደር አዝማሪ አዚሟል። ዛሬም ይህ ግጥም የብዙ ባህላዊ ዘፈኖች አዝማች ነው። ደጃች አያሌው ብሩ ደፋር ናቸው ይባላል። ከአጼ ኃይለሥላሴ ጋር ቢቀያየሙም በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ሲመጣ ቅድሚያ ለአገሬ ብለዋል። ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘው የዶክተር ሀራልድ ናይስተሮም (ትርጉም ገበየሁ ተፈሪ እና ደሳለኝ አለሙ) መጽሐፍ እንደተጠቀሰው ደጃች አያሌው “ንጉሡ እንደኛ ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ ግን የሁላችንም ናት" ብለው ጦራቸውን መርተው በሽሬ ግንባር ዘምተዋል። ጉዟችን ቀጥሏል። ደባትን እያለፍን ነው። ‘እንኳን ደህና መጡ፤ ወደ ጭና ታሪካዊቷ ሥፍራ’ የምትለዋን ታፔላን በስተግራ እያየን ወደ ደባርቅ ገሰገስን። የሰሜን ተራሮች የብርድ ወጨፎ ያረሰረሳትን ደባርቅን ከማለፋችን ሊማሊሞ ጠመዝማዛ ቁልቁለት ተቀበለን። አስፈሪ የሊማሊሞ መልክዓ ምድር የደጋው ሰሜን ውርጭ እና የተከዜ በርሃ ኬላ ነው። ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድህን “የሰማይ የምድሩ ኬላ፣ የየብስ የጠፈሩ ዋልታ አይበገር የዐለት ጣራ፣ አይመክተው መከታ ሊማ-ሊሞ አድማስ ሰበሩ፣ በጎማ ፈለግ ይፈታ? በትሬንታ እግር ይረታ?…” ብሎ የመኪና መንገድ ተገንብቶበት በማየቱ ግርምቱን የተቀኘለትም ለዚህ ይመስላል። ከሊማሊሞ ቁልቁለት በኋላ አዲ-አርቃይ፣ ዛሪማ፣ ማይፀብሪ እና ሌሎች የጠለምት ወረዳ ከተማዎችን አልፈን፤ የዋልድባ ረባዳማ አካባቢዎችን ተሻግረን ተከዜ ወንዝ ደረስን። የዚህን መንገድ እና ተከዜ ወንዝን ሳስብ የሀዲስ ዓለማየሁ ትዝታ አስተከዘኝ። የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ጦር የወገንን ጦር ፊት ለፊት መቋቋም ሲሳነው በሰው ልጆች ላይ ተደርጎ የማያውቅ መርዝ በጅምላ የፈጀበት አሳዛኝ ታሪክ ነበር። በተከዜ ወንዝ ውሃን በመመረዝ የወገን ጦር ያለቀበት ሥፍራ ነው። የተከዜ ሸለቆ በኢትዮጵያዊያን ደምና አጥንት ዋጋ የተከፈለበት ነው። ሀዲስ ዓለማየሁ በአንድ ዕለት የተመለከቱትን እንዲህ ጽፈውታል። “የተከዜ ውሀ እመሻገሪያው ላይ ሰፊና ፀጥ ያለ ነው። ታዲያ ያ ሰፊ ውሀ፤ ገና ከሩቅ ሲያዩት ቀይ ቀለም በከባዱ የተበጠበጠ ይመስላል። “ምን ነገር ነው፤ ምን ጉድ ነው?” እየተባባልን ቀረብ ስንል መሻገሪያው በቁሙም በወርዱም ከዳር እስከ ዳር ሬሳ ሞልቶበት የዚያ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው። የሰው ሬሳ፣ የፈረስ እና የበቅሎ ሬሳ፣ ያህያ ሬሳ፣ ያውሬ ሬሳ፥ ሬሳ ብቻ! እግር ከራስ ራስ ከእግር እየተመሰቃቀለ እየተደራረበ ሞልቶበት፥ የዚያ ሁሉ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው”። ይሉናል። ቀጥለውም “በእውነቱ እንዲህ ያለውን መሳሪያ ምንም ጠላት ቢሆን በሰው ላይ ለማዋል የሚጨክን ሰው፥ ሰብዓዊ ስሜት የሌለው፣ አለት ድንጋይ የተፈጠረበት መሆን አለበት፤ እንዲህ ያለውን መሳሪያ በሰው ላይ ማዋል ሰብዓዊ ህሊና ሊሸከመው የማይችል እጅግ ከባድ መሆኑን ዓለም ሁሉ ያወቀውና ያወገዘው በመሆኑ የኢጣሊያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ከማድረጉ በቀር “ሌላ መንግሥት በሌላ አገር ላይ አደረገ’ ሲባል ተሰምቶ የሚያውቅ አይመስለኝም” ብለዋል። ከተከዜ ባህር ማዶ ጉዞዬ ያገኘኋት ሌላዋ ታሪካዊ ሥፍራ እንዳባጉና ናት። እንዳባጉና የወገን ጦር ትልቅ ገድል የፈጸመበት ነው። ጀግኖች አባቶቻችን የጠላት ታንክ ሳያስፈራቸው የጠላት ጅምላ ጨራሽ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ተቋቁመው ጠላትን ድባቅ የመቱበት፤ ወደ አክሱም እንዲያፈገፍግ ያደረጉበት ሥፍራ ነው። “የጠላት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በጦር ሜዳው ትንንሽ ቦምቦች አውቶማቲክ ጠመንጃ ይተኩስ ነበር። አቢሲኒያኖች ደግሞ ከጠላት ጋር ግብግብ ገጥመው ጉዳይም አልሰጡትም ነበር…” ይላል ዶክተር ሀራልድ ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘ መጽሐፉ። ይህ አካባቢ በሀገር ፍቅር የነደዱ ኢትዮጵያዊያን ደም ያፈሰሱበት፣ አጥንት የከሰከሱበት፤ ለኢትዮጵያ መስዕዋትነት የከፈሉበት ነው። ይህ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ቀጣና ነው። ቀኑ ተገባዷል። ጉዟችን እንደቀጠለ ነው። እኔም የማሽላ ማሳዎችን ግራ ቀኝ እየተመለከትኩ ለዕለቱ መዳረሻችን ወደሆነችው ሽሬ ከተማ ገባን። ሽሬ በትግርኛ ‘ሽረ’ ሲሉት ይደመጣሉ። በእርግጥ ሽሬን ለመጀመሪያ ጊዜ መርገጤ ነው። ዕለቱም ጥር ሥላሴ ነው። ሽሬ በጥር ሥላሴ ትደምቃለች፤ ሙሉ ስሟም ሽረ እንዳስላሴ ነው። የሽሬ ሥላሴ ጠበል ሽሬ ደርሰን ማረፊያችንን ያዝን። ጊዜው በጣም አልመሸምና ከተማዋን በቀላሉ መቃኘት ይቻላል። ሽሬ ሰፊና ደማቅ የዞን ከተማ ናት። ከመካከላችን የአንደኛው ባለሙያ ቤተሰቦች ሽሬ ነበሩና አስጠሩን። ለሥላሴ ጠበል ግብዣ። ባል እና ሚስቱ ከልክ በላይ መስተንግዶ አደረጉልን። ‘ጠብ እርግፍ አድርገው አስተናገዱን’ ማለት ይቀላል። እንግዳ መቀበል ነባር ኢትዮጵያዊ እሴታችን ቢሆንም ጦርነት ውስጥ ለቆየ አካባቢ የተለየ መልክ ነበረው። እንግዳ አቀባበላቸው በእርግጥም የመሃል አገር ሰው የናፈቃቸው ይመስላል። የተትረፈረፈ እህልና ውሃ አቅርበው በ’ብሉልን፤ ጠጡልን’ ተማጽኗቸው የተነፋፈቀ ቤተ-ዘመድ ግብዣ አስመሰሉት። የሥላሴው ጠበል የሸሬ ጠላ ቀረበ። የሸሬ ጠላ ሳስታውስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ታወሱኝ። የወቅቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምሀሩ ፕሮፌሰር ሽብሩ በዘመነ ደርግ በዕድገት በሕብረት ዘመቻ ተማሪዎቻቸውን ይዘው ሽሬ ዘምተው ነበር። በወቅቱ ታዲያ የሸሬ ጠላ ፍቅር ይዟቸው በየጊዜው ሲኮመኩሙ የተመለከቱ ሰዎች ‘ፕሮፌሰሩ ከጠፉ የሚገኙት ጠላ ቤት ነው’ ሲባሉ እንደነበር ‘ከጉሬ ማርያም እስከ አዲስ አበባ’ በተሰኘው ግለ ታሪካቸው አስፍረዋል። ከግብዣ መልስ ከማረፊያ ሆቴል ላይ ሆኜ ከተማዋን ስቃኛት ከጦርነት ድባቴ የተላቀቀች ይመስላል። የአመሻሽ ሕዝቡ እንቅስቃሴም ሆነ እስከ ሌሊቱ አጋማሽ የሚሰሙ የመዝናኛ ቤቶች ሙዚቃዎች የከተማዋን አሁናዊ መልክ የገለጠልኝ ነበር። ንጋት ላይ በቁርስና ቡና ሰዓታት ከሰዎች ጋር መስተጋብሬ ጀመረ። በጦርነት አዙሪት የከረመችው ሽሬና አካባቢው ኑሮ እጅጉን የከበደ ነበር። መልከ-ብዙ ማህበራዊ ቀውሶች አስተናግደዋል። አሁናዊ ምላሻቸው “ተመስገን፤ ያ ሁሉ አለፈ” የሚል ነው። ገበያው ተረጋግቷል፤ ማህበራዊ ኑሮ ተመልሷል። ድህረ-ሰላም ስምምነት ለሽሬ ነዋሪዎች ሁለንተናዊ እፎይታን አንብሯል። ከቀናት በኋላ በአክሱም የታዘብኩትም እንዲህ ነው። ኑሮን ያቀለለው የተቋማት አገልግሎት ጅማሮ በመጀመሪያ ዘገባ ስራዬ መሰረተ ልማትን አገልግሎት ቃኘሁ። ባንክ፣ ቴሌ፣ ሆስፒታል… መሰሎቹን። ተጠቃሚዎችንም፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ስራ ሃላፊዎችንም አነጋገርሁ። ከሰላም ስምምነቱ ማግስት ጀመሮ ተቋማቱ ወደስራ መመለሳቸው ከሁለንተናዊ ችግር እንደታደጋቸው ያነሳሉ። በትራንስፖርት እየተንቀሳቀሱ፣ በኤሌክተሪክ ስራዎቻቸውን እየከወኑ ነው። ለሁለት ዓመታት የተቋረጠው አገልግሎት አቅርቦት እና የአገልግሎት ፈላጊዎች ፍላጎት ግን አሁንም ሙሉ በሙሉ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ የተጠቃሚዎችም፤ የአገልግሎት ሰጭዎችም ሀሳብ ነው። በሽሬ ስሁል ሆስፒታል የተመለከትኳቸው፤ ያነጋገርኳቸው፤ ከታዳጊዎች እስከ አዛውንት ዕድሜ ያሉ ህሙማን የሰላም አየር ማግኘታቸው የሕይወታቸው ዑደት እንዲቀጥል አድርጓል። ድንገተኛም ሆነ ነባር ህመም ያለባቸው ሰዎች በነጻ እየታከሙ ነው ያገኘኋቸው። ሰላም ከሌለ መታከም ቀርቶ በቅጡ ማስታመም፤ በወጉ መቀበርም እንደማይቻል ገልጸውልናል። የጤና፣ የባንክና የቴሌኮም አገልግሎት የግብዓት ክፍተቶች የማሟላት ሰራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም በፌዴራል ደረጃ በየተቋማቱ የተመደቡ አስተባባሪዎች አረጋግጠውልኛል። የጸጥታ አካሉና የህብረተሰቡ ትብብርም የሚያስቀና እንደሆነ ግለሰቦችም፤ የጸጥታ አካላትም ነግረውኛል። አክሱም ጺዮን ማርያም፣ ሽሬ ስላሴ ንግስ፣ የጥምቀት በዓላት ከሶስት ዓመታት በኋላ በአደባባይ ታቦት ወጥቶ ተከብሯል። የፌዴራል ፖሊስ ተወካዮችም ይህንኑ ነው ያረጋገጡልኝ። የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከከተማ ነዋሪዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት ቤተሰባዊ የሆኑ ይመስላል። እንቅስቃሴያቸውም የሰላማዊ ቀጠና መልክ ያለው ነው፤ ዩኒፎርም ከመልበሳቸው በስተቀር ጀሌያቸውን ይንቀሳቀሳሉ። ይህ ደግሞ መተማመን ከመፍጠር ባለፈ ጦርነት ውስጥ ለቆየ ማህበረሰብ ከስነ ልቦና ጫና እንዲላቀቅ አይነተኛ ሚና እንደላው ይሰማኛል። ኢ-መደበኛ የሽሬና አክሱም ወጎች ያረፍኩበት ሆቴል ባለቤት ‘አደይ’ ተግባቢ ናቸው። ደግ እናት ይመስላሉ። ከገባን ጀምሮ ‘ጠላ ተጎንጩ፤ ቡና ጠጡ’ ጭንቃቸው ነው። ሁለት ቀን ቡና አስፈልተውልናል፤ ጠላ አቅርበው ዘክረውናል። ይህ ሁሉ ሲሆንም ለከተማው እንግዳ መሆናችንን እንጂ ስለሙያችንም ሆነ ስለሌላ ማንነታችን አያውቁም ነበር። ብዙ መጨዋወትና ውሎ አዳር በኋላ ነው ጋዜጠኛ ስለመሆናችን ያወቁት። አደይ ተጨዋች ናቸው። አማርኛ ያዝ ቢያደርጋቸውም ጨዋታቸው ‘ኩርሽም’ ነው- ተሰምቶ የማይሰለች። በአጋጣሚ ‘ሰለክላካ’ ስለምትባለዋ ታሪካዊ ሥፍራ ጠይቄያቸው እያወጋን ነበር። ‘እንደእናንተ ወጣቶች ሳለን ‘ሰለክላካን ያላዬ ሸዋን ያመሰግናል’ ይባል ነበር። ታዲያ አንድ የሸዋ ሰው መጣና ሰለክላካን አየና ‘በቃ ይቺ ናት’ ሰለክላካ’ ብሎ ተገረመ” ብለው አሳቁን። (የፍቅር እስከ መቃብር መሪ ገጸ-ባህሪው ‘በዛብህ’ ወደ ዲማ ጊዮርጊስ ሄዶ ‘የዲማ መልኳ እና ዝናዋ’ ተጣርሶበት እንደተገረመበት ቅጽበት መሆኑ ነው)። አደይ የተጀመረው ሰላም ፍጹም ምሉዕ ሆኖ ወደ ቀደመ ኢትዮጵያዊ መልካችን የምንመለስበት ጊዜ እንዲመጣ ይሻሉ። ከጦር-ነት ወደ ሰላም-ነት! ቆንጂዬዋ ፊዮሪ የኮሌጅ ተማሪ ነበረች። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጀምሮ በኋላም በጦርነት ሳቢያ ትምህርቷን ካቆመች ሦስት ዓመታት ሆኗታል። ጦርነቱ ከቆመ በኋላ የጀበና ቡና ጀምራለች። ደንበኞቿ ሰብሰብ ብለን እንቀመጣለን። ፊዮሪ ከስኒ ማቅረቢያዋ ላይ አነስተኛ ጀበናዋን፤ የሚያማምሩ ስኒዎቿን እና መዓዛው ከሚያውድ የዕጣን ማጨሻዋ ጋር ሰድራ ይዛ ትቀርባለች። ከመካከላችን ካለው ጠረጴዛ ላይ ታስቀምጥና እርሷም ወንበር ይዛ ከመካከላችን ትቀመጣለች። ቡናው እስኪሰክን ጨዋታዋን ታስኮመኩመናለች። ቡናው ከሰከነ በኋላ ቡናዋን ቀድታ ለእያንዳንዳችን በእጃችን እያነሳች ትሰጣለች። በሽሬ ቡና የሚቀርበው በዚህ መልክ ነው። ለፊዮሪ እና መሰሎቿ ጦርነቱ ክፉ ጠባሳ መጣሉ፤ ተስፋቸው ላይ መጥፎ አሻራ ማስቀመጡን ታነሳለች። አሁን ግን ብሩህ ተስፋ ሰንቃለች። ስለነገዋም “ሰላሙ ይዝለቅልን፤ ትምህርቴን ለመቀጠል እመኛለሁ” ትላለች። አክሱም ከሽሬ በስተሰሜን 60 ኪሎ ሜትር ይርቃል። ከሽሬ አክሱም ስንንቀሳቀስ ከጥምቀት ዕለት በስተቀር ገበሬው የግብርና ሥራዎቹን እየከወነ ነበር። አርሶ አደሩ ያርሳል፤ መስኖውን ያለማል። የተዘራውን ውሃ ያጠጣል። የበቀለ ቡቃያውን ይኮተኩታል። ከጦርነት ወደ ልማት መዞሩን ዐይኔ ታዝቧል። በጥምቀት ዋዜማ፤ የከተራ በዓል ዕለት ሁለት ጎራማይሌ የረፋድ ትዕይንቶችን ላንሳ። ከአክሱም ከተማ ወደ አድዋ እና ሽሬ መገንጠያ አካባቢ ሰፊ የቀንድ ከብት ገበያ ነበር። እውነተኛ የዓመት በዓል ገበያ መልክ ያለው ትዕይንት ነበር። በተለይም የፍየል ዋጋ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተገበያዩ እንደነበር ሰምቻለሁ። ታሪካዊቷን አክሱም ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ የረገጥኳት/የተሳለምኳት ከአራት ዓመት በፊት በ2011 ዓ.ም ይመስለኛል። ከገበያው ቀጥሎ በታቦተ-ጽዮን መገኛዋ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ደጅ፣ በጥንታዊያኑ የአክሱም ሐውልት መገኛ አደባባይ ነበር። ከጽዮን በስተምዕራብ በአርባቱ እንሰሳ በኩል፤ በቅዱስ ያሬድ ዋርካ… አድርጌ በጽዮን ዋናው በር ደረስኩ። ማራኪ የአክሱም የኮብልስቶን መንገዶች ኦና ናቸው። የወትሮው ግርግር ናፍቋቸዋል። ከጽዮን ቅጥር ግቢ በዋናው በር በስተውጭ አነስተኛ እና ብቸኛ ዋንዛ በኮብልስቶን መሃል ነበረች። ዛሬም ለምልማ አለች። በዚህ አካባቢ ድሮ የነጭ ጎብኚ ጋጋታ፣ የጽዮን ደጅ ጠኚ ምዕመን… የተጨናነቀ ነበር። እንደ ድሮው የፎቶ አንሺ ግርግር፣ የአክሱም መስቀል ቀርጸው የሚሸጡ ወጣቶች ጫጫታ የለም። ይልቁንም እርጥባን የሚሹ አቅመ ደካሞችና ህፃናት ነበሩ። ጦርነት የሥፍራዋን መልክ አጠይሞታል። ያም ሆኖ ከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ሙሉ በኩሉሄ ባይባልም ወደነበረበት እየተመለሰ ነው። የግልም ሆነ የመንግሥት ባንኰች ሥራ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከአክሱም ሐውልት ወደ ሌላ ሰፈር አቀናሁ። ትርሐስ ገና ታዳጊ ልጅ ነች። ጠይም፤ ስርጉድ፣ ሳቂታና ተረበኛ አይነት ልጅ ነች። እንደ ሽሬዋ ፊዮሪ መንገድ ዳር የጀበና ቡና እየሰራች ነው። ከሩቅ የመጣን እንግዶች መሆናችንን ስታውቅ፤ ደስታዋ ከገጿ ይነበብ ነበር። ያለፉ ጊዜያትን ሰቆቃ አጫወተችን። ስለቀጣይ ዕጣ ፈንታዋ እና ዕቅዷ ስታወራ ትቆይና “የሰው ልጅ ግን በጣም ከሃዲ ነው። ከወራት በፊትኮ ስለቢዝነስ አላስብም ነበር። መቼ እሞታለሁ እንጂ” ብላ ራሷን ትወቅሳለች። ወደ ሰማይ አንጋጣ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች። ጦርነት ተራውንም ሕዝብ ለመልከ-ብዙ ቀውስ ዳርጎት እንደቆየ ታነሳለች። ዛሬ ሁሉ አልፎ ሰላም መውረዱ ለመጨዋወት መብቃቷ ለእርሷ ትልቅ ብሥራት ነው። ይህ ለትርሐስ ብቻ ሳይሆን ለመላው አክሱማዊያን መሆኑ እሙን ነው። አክሱም ከተማ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ከዋለችበት ጊዜ ጀምሮ በከተማዋ በሻለቃ አዛዥነት የተሰማራ የፌደራል ፖሊስ አባልም ያጋጠመውን አሳዛኝ ገጠመኞች አጫውቶኛል። ጦርነቱ ቢራዘም ኖሮ በተራው ሕዝብ ላይ ምን ያህል የከፋ ጉዳት ይደርስ እንደነበር በአሳዛኝ ሁኔታ ገልጾልኛል። አክሱሞች ያን ሁሉ አልፈው ሰላም አየር ነፍሶ፣ ከስጋት ቆፈን ተላቀው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ተመልሰዋል። የዛሬ ሳምንት ሰርክ(11 ሰዓት) ላይ አክሱም የከተራ በዓል በድምቀት አክብራለች። ታቦተ-ጽዮን ወደ ባህረ- ጥምቀቱ ስትወርድ፤ ወግና ሥርዓቱ ተጠብቆ፣ ሕዝቡ በሀበሻ ነጫጭ አልባሳት፣ ካህናት በልብሰ ተክህኖ ደምቀው … እየተከወነ ነበር። አንዲት እናት ለአማርኛ ተናጋሪ በቀረበ አነጋገር እያለቀሱ ታቦት እየሸኙ ነው። ትኩር ብዬ ሳያቸውም ዕንባቸው ዱብ ዱብ ይላል። “ከዚያ ሁሉ መከራ አልፎ ለዚህ በቃን፤ ተመስገን” እያሉ እልልታውን ያቀልጡታል። በደስታ እያነቡ ነበር። ይህ ስሜት የብዙኃኑ አክሱማዊያን እናቶች እንደሆነ መገመት ቀላል ነው። አክሱም በኮቪድ እና በኋላም በጦርነቱ ምክንያት ባህረ-ምቀት ታቦት ወጥቶ ሲከበር ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ከወትሮው በተለየ ድምቀትና ውበት በሰላምና በደስታ፤ በአደባባይ እልልታና ሆታ በማክበራቸው ልዩ ስሜት ፈጥሮባቸዋልና! እናም በአክሱም የከተራ ሆነ የበዓለ-ጥምቀት ክብረ-በዓላት በሰላም ስምምነቱ ማግስት በድምቀት ተከውኖ አለፈ። የሃይማኖት አባቶቹም ሆኑ ምዕመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅም የዘንድሮው ክብረ-በዓል ካለፉት ዓመታት ነባራዊ ሁኔታ ጋር እያነጻጸሩ፤ ትልቅ ብሥራትና መልክ እንዳለው ገልጸዋል። ሰላም እንዲጸና፤ ነባር ኢትዮጵያዊ አንድነትና መተባበር እንዲመለስ ጽኑ መሻታቸውን ነግረውናል። በበጎ ቀን የማውቃትን አክሱም፤ ከረዥም ጊዜ በኋላ አሁናዊ መልኳን ታዝቤ፤ የነገ ትዝታ ሰንቄ ተመለስኩ!! ሰላም ለኢትዮጵያ!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም