በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መቻል፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሃዋሳ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል - ኢዜአ አማርኛ
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መቻል፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሃዋሳ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 5/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ተደርገዋል።
መቻል ሸገር ከተማን 3 ለ 0 አሸንፏል። ትዕግስት ወርቁ፣ ስንታየሁ ኤርኮ እና ቤተልሄም መንተሎ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
በሌላኛው መርሃ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ልደታ ክፍለ ከተማን 3 ለ 1 አሸንፏል።
ዳግማዊት አለማየሁ ሁለት ግቦችን ስታስቆጥር ንግስት ኃይሉ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፋለች።
አስራት አለሙ ለልደታ ክፍለ ከተማ ብቸኛዋን ጎል አስቆጥራለች።
ሃዋሳ ከተማ በታደለች አብርሃም ጎል ባህር ዳር ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል።
ጨዋታዎቹን ተከትሎ የሶስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል።