አርእስተ ዜና
በክልሉ ከህዝብ ቁጥር ጋር የሚጣጣም የኢኮኖሚ እድገት እንዲኖር ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው
Jul 1, 2025 61
ሀዋሳ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ከህዝብ ቁጥር ጋር የሚጣጣም የኢኮኖሚ እድገት እንዲኖር ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ገለፀ። ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የክልሉን የሥነ-ህዝብ ምክር ቤት ጉባኤ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ዛሬ አካሂዷል፡፡ የቢሮው ኃላፊ አራርሶ ገረመው(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ በክልሉ የህዝብ ቁጥር እየጨመረ ከመምጣት ባለፈ ከፍተኛ የህዝብ ጥግግት አለ፡፡ በየጊዜው እያደገ ከሚመጣው የህዝብ ቁጥር ጋር የሚጣጣም የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገቡ ለመቀጠል ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ለዚህም ቢሮው ከግብርና፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከአገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች ጋር ተባብሮ በመስራት እየተመዘገበ ያለውን የኢኮኖሚ ዕድገት ከህዝብ ቁጥር ዕድገት ጋር ለማጣጣም እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የህዝብ ቁጥርን ወደ መልካም ዕድል በመቀየር በእውቀት የበቁ ዜጎችን ለማፍራት፣ ህዝቡ ከቴክኖሎጂ ጋር ያለውን ቁርኝት ለማሳደግ፣ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመርና ለመሰል ሥራዎች ቢሮው ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅት የሴክተር ተቋማትን የአምስት ዓመታት አጠቃላይ ዕድገት ጠቋሚዎች ዝርዝር የያዘ የመረጃ ቋት መዘጋጀቱን ጠቅሰው፣ ይህም ባለድርሻዎች በተደራጀ መረጃ ላይ የተመሰረተ ሥራ ለመስራት ያስችላቸዋል ብለዋል፡፡ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዘማች ሂርጢባ የግብርናው ሴክተር ከክልሉ ጥቅል ምርት እድገት ከ43 በመቶ በላይ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ የሚመዘገበውን ዕድገት ለማስቀጠልና የህዝብን ቁጥር ታሳቢ ያደረገ የግብርና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ከፕላንና ልማት ቢሮ ጋር ተናበን እየሰራን ነው ሲሉም ገልጸዋል። በክልሉ ያለውን የእርሻ መሬት መጠን የመለየት ሥራ መከናወኑን ጠቁመው ለእርሻ ሥራ በቂ መሬት የሌላቸውን በእንስሳት ልማትና በሌሎች ሥራዎች እንዲሰማሩ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።፡ የሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ ግብዓት ጥራት ቁጥጥር አግልግሎት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ቡሪሶ ቡላሾ በዕቅድ የሚመራ ቤተሰብ እንዲኖርና የመኖር ምጣኔው ከፍ ያለ ማህበረሰብ ለመገንባት በትብብር ይሰራል ብለዋል፡፡ በዚህ ረገድ የተያዙ ግቦችን ለማሳካት የጤና መሠረተ ልማቶችን የማስፋፋት እንዲሁም ግብዓቶችን በበቂ ሁኔታ የማሟላት ሥራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ነው ያሉት፡፡ በዚህም በክልሉ የመኖር ምጣኔን ከተቀመጠው የመኖር ምጣኔ ጋር ማጣጣም መቻሉን ጠቅሰው፣ የወሊድ ምጣኔንም ወደ 3 ነጥብ 91 ማውረድ ተችሏል ብልዋል።፡ በጉባኤው የሚመለከታቸው ሴክተር ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የባህል ሽማግሌዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በሸገር ከተማ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - አስተዳደሩ
Jul 1, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ። በከተማው በኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዛሬ ተጀምሯል። በከተማው በበጀት ዓመቱ ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ የተገነቡ የመሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።   የከተማው ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) በምረቃ ሥነስርዓቱ እንደገለጹት የከተማዋን ልማት በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው። በበጀት ዓመቱ በ17 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር 384 ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው፣ ከእነዚህ ውስጥ የ308ቱ ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ በቅተዋል ብለዋል። ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል የመስኖና የመጠጥ ተቋማት፣ ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣቢያ፣ መንገዶች፣ ፖሊስ ጣቢያ እና የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች ግንባታን በማሳያነት ጠቅሰዋል።   የኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ ሀላፊ ጫላ ደሬ በበኩላቸው ለህብረተሰቡ የልማት ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ለመስጠት ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ በክፍለ ከተማው ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ 24 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ሥራ መጠናቀቁን ተናግረዋል። የህዝብን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፣ ህዝቡም ለፕሮጀክቶች ስኬታማነት እያደረገ ያለውን ተሳትፎ እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል። ከልማት ፕሮጀክቶቹ ምረቃ በተጨማሪ የከተማው ነዋሪዎችን ያሰተፈ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በከተማው ኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ ድሬ ሶኮሩ ወረዳ ዛሬ ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) እንዳሉት በክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ከ40 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ለምግብነት፣ ለደንና ለውበት የሚውሉ ችግኞች ይተከላሉ።   በተመረጡ ክፍለ ከተሞችም የአቮካዶና የአፕል ችግኞችን በመትከል በክልስተር የማልማት ስራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል። በችግኝ ተከላው ከተሳተፉ የኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ በቀለ ያኢ እና አቶ በላቸው አበራ ችግኝ ከመትከል ባለፈ በየጊዜው በመንከባከብ ለማሳደግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ መትከል የአየር ንብርት ለውጥን ለመቋቋምና ምርታማነትን ለማሳደግ ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ በየዓመቱ በአረንጓዴ አሻራ ልማት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ችግኝ በመትከል አሻራቸውን ማኖራቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸው፣ በቀጣይም የተከሏቸውን ችግኞች በመንከባከብ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል።
አዋጁ በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች መብታቸውና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የሚያስችል ነው
Jul 1, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች መብታቸውና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የሚያስችል መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 41ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅን መርምሮ አጽድቋል፡፡ አዋጁን አስመልክቶ የተዘጋጀውን የውሳኔ ሀሳብ በምክር ቤቱ የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) አቅርበዋል፡፡ በዚህም አዋጁ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በተመለከተ ቀደም ሲል ሲሠራባቸው የነበሩት አዋጆች ክፍተቶች የነበሩባቸው በመሆኑና በጊዜ ሂደት አዋጆቹ ያላካተቷቸውን ጉዳዮችን በመለየት ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል አዋጅ እንደሆነ ተናግረዋል። የቀድሞዎቹ አዋጆች የቤት ውስጥ ሠራተኛ፣ የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ ውጭ የትምህርት ዝግጅት የማይጠይቁ የሥራ ዓይነቶችን ባለማካተታቸው ክፍተቶች የተፈጠሩ ስለመሆኑም አንስተዋል። አዋጁ ሕገ- ወጥ የውጪ ሀገር የሥራ ስምሪትን ለመከላከልና በውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት የዘመነ የአንድ ማዕከል የአሠራር ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚያስችልም ጠቅሰዋል፡፡ በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች መብታቸውና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የሚያስችል ላኪ ኤጀንሲዎች ተመጣጣኝ የዋስትና ገንዘብ እንዲያስቀምጡ በማድረግ የዜጎችን እንግልት የሚያስቀር አዋጅ በመሆኑ ነው ብለዋል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ዜጎች ለህገ ወጦች ሳይጋለጡ በአግባቡ ሰልጥነው ተመዝነው እንዲሰማሩ የሚያደርግ ነው ብለዋል።   በአዋጁ ጠንካራ የሆነ የስልጠናና የምዝና ስርዓት እንደ አንድ ጠንካራ ስርዓት ተደርጎ መካተቱን ሚኒስትሯ ተናግረዋል።     የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ አዋጁ ዜጎችን ከህገ ወጥ ደላሎች የሚታደግና የዜጎችን ክብርና ደህንነት የሚያስጠብቅ ነው ሲሉ ተናግረዋል።  
የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው
Jul 1, 2025 59
  አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ። አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ በስፔን ሲቪያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በኮንፍረንሱ እየተሳተፈ ነው። ሚኒስትሩ በኮንፍረንሱ ባደረጉት ንግግር ከ10 አመት በፊት በአዲስ አበባ ሶስተኛው ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይሁንና በኮንፍረንሱ የጸደቀው የአዲስ አበባ የድርጊት መርሃ-ግብር የአተገባበር ተግዳሮት እንደገጠመው ጠቅሰው የሲቪያ ስምምነት ይህንን ተግዳሮት የሚሻገር መሆን እንደሚገባው አመልክተዋል። ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመተግበር ከሚያስፈልገው ፋይናንስ ውስጥ የ4 ትሪሊዮን ዶላር እጥረት መግጠሙን አንስተዋል። ይህ ሁኔታ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራትን ለዘርፈ-ብዙ ተግዳሮቶች ዳርጓቸዋል ነው ያሉት ሚኒስትሩ። ለአብነትም አዳጊ ሀገራት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ ለሚመጡ ቀውሶች እና ለእዳ ጫና መጋለጣቸው አሳሳቢ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ኮርፖሬሽኖች ላይ ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ የታክስ ስርዓትን መተግበርና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጥላ ስር በየነ-መንግስታዊ የብድር አስተዳደርን በማቋቋም ዘላቂ ያልሆነ የብድር ችግሮችን መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል። በተጨማሪም የልማት ፋይናንስ ድጋፎችና ብድሮች ሀገራት ቅድሚያ ከሚሰጣቿው ጉዳዮችና እቅዶች ጋር መጣጣም እንዳለባቸውና አዳጊ ሀገራት የሚያገኙት የፋይናንስ ድጋፍ መጨመር እንዳለበት አመልክተዋል። በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ዘላቂ እና ተገማች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖራቸውና ቀውሶችን በተገቢው መንገድ ማስተዳደር እንዲችሉና ዓለም ዓቀፍ የልማት ፋይናንስ ስምምነቶች በተገቢው እንዲተገበሩ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ሊኖር እንደሚገባም ነው የገለጹት። በአፍሪካ እና በአጠቃላይ አዳጊ ሀገራት በመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ የስራ ዕድል ፈጠራና የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የሚያስችል የፋይናንስ አቅርቦት በአስተማማኝ መልኩ ማቅረብ ድህነትን ለመቀነስ እና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ሚኒስትሩ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን “ዓለም አቀፍ ትብብርን በአዲስ መልክ ማደስ” በሚል ርዕስ በሚኒስትሮች ደረጃ በተደረገው ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል። ሁለተኛው ቀኑን የያዘው አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ልዑክ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን እየተካሄዱ ባሉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል።
በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል
Jul 1, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞችን በሕግ ተጠያቂ ማድረጉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተካሂዷል። የወንጀል ምርመራ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊና የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሙስና፣ በህገ ወጥ የሰዎችና የጦር መሳሪያ ዝውውር፣ በኮንትሮባንድና አደንዛዥ ዕጽ ዝውውር የተጠረጠሩ ሰዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል በህግ ተጠያቂ መደረጋቸውን አስታውቀዋል። ኮሚሽኑ ሕግን ለማስከበር በወሰደው እርምጃ 1 ሺህ ተጠርጣሪዎች ላይ የተለያየ መጠን ያለው የቅጣት ውሳኔ መተላለፉን አንስተዋል። በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር የተሳተፉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ በማድረግና የምርመራ መዝገብ በማጠናቀቅ ለጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ቀርቦ ክስ እንዲመሰረትባቸው መደረጉን ተናግረዋል። እነዚህ ተጠርጣሪዎች ሀሰተኛ መታወቂያና በርካታ ሲም ካርዶችን በመጠቀም፣ ሆቴሎችና ማረፊያ ቤቶችን በመከራየት ዜጎችን በማጭበርበር ላይ ተሰማርተው የነበሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዚህም በድርጊቱ ላይ የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞች ላይ ምርመራ አድርጎ ክስ በመመስረት ወደ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ መደረጉንም አብራርተዋል። ከሀገር ውስጥና ከውጭ ኃይሎች ጋር በማበር በሽብር ወንጀል የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት እንዲሁም ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በመሆን ለሕግ የማቅረብ ሥራ መከናወኑንም አስረድተዋል። በዚህም ከ450 በላይ ተጠርጣሪዎች በሰነድና በሰው ማስረጃ በማጣራት ክስ እንዲመሰረትባቸው የተደረገ ሲሆን በህግ ተጠያቂ መሆናቸውንም ገልጸዋል። በኮንትሮባንድና ሕገ ወጥ ጦር መሳሪያ ዝውውር ላይ የተሳተፉ 143 ተጠርጣሪዎች ለሕግ መቅረባቸውን ጠቁመው ካናቢስ፣ ኮኬይንን ጨምሮ የተለያየ መጠን ያላቸው አደንዛዥ ዕጾች ዝውውር ወንጀል የተሳተፉ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ውለው ተጠያቂ ተደርገዋል ብለዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ በበጀት ዓመቱ ከ6 ሺህ በላይ የምርመራ መዝገቦች ምርመራ ተጠናቆ ለፍትህ ሚኒስቴር የተላከ ሲሆን በዚህም በሀገርና በህዝብ ላይ ጉዳት በማድረስ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። አቶ ሙሊሳ አክለውም በዘረ መል/DNA/ ምርመራ ዘርፍም ከ300 በላይ የምርመራ ጉዳዮች መቅረባቸውን አስታውሰው ወቅቱንና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ምርመራ ተከናውኖ የተገኘው ውጤት ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል። አጭበርባሪዎች ከባንክ የተደወለ በማስመሰል እያጭበረበሩ መሆኑን የገለጹት ሃለፊው ከባንክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም ዓይነት የባንክ አገልግሎት እንደሌለ ዜጎች ሊገነዘቡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ዜጎች የሚስጥር ቁጥራቸውን ለሶስተኛ ወገን አሳልፈው መስጠት የለባቸውም ያሉት አቶ ሙሊሳ ህብረተሰቡ የአጭበርባሪዎች ሰለባ እንዳይሆን ሊጠነቀቅ እንደሚገባ አመልክተዋል።
የሚታይ
አዋጁ በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች መብታቸውና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የሚያስችል ነው
Jul 1, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች መብታቸውና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የሚያስችል መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 41ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅን መርምሮ አጽድቋል፡፡ አዋጁን አስመልክቶ የተዘጋጀውን የውሳኔ ሀሳብ በምክር ቤቱ የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) አቅርበዋል፡፡ በዚህም አዋጁ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በተመለከተ ቀደም ሲል ሲሠራባቸው የነበሩት አዋጆች ክፍተቶች የነበሩባቸው በመሆኑና በጊዜ ሂደት አዋጆቹ ያላካተቷቸውን ጉዳዮችን በመለየት ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል አዋጅ እንደሆነ ተናግረዋል። የቀድሞዎቹ አዋጆች የቤት ውስጥ ሠራተኛ፣ የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ ውጭ የትምህርት ዝግጅት የማይጠይቁ የሥራ ዓይነቶችን ባለማካተታቸው ክፍተቶች የተፈጠሩ ስለመሆኑም አንስተዋል። አዋጁ ሕገ- ወጥ የውጪ ሀገር የሥራ ስምሪትን ለመከላከልና በውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት የዘመነ የአንድ ማዕከል የአሠራር ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚያስችልም ጠቅሰዋል፡፡ በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች መብታቸውና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የሚያስችል ላኪ ኤጀንሲዎች ተመጣጣኝ የዋስትና ገንዘብ እንዲያስቀምጡ በማድረግ የዜጎችን እንግልት የሚያስቀር አዋጅ በመሆኑ ነው ብለዋል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ዜጎች ለህገ ወጦች ሳይጋለጡ በአግባቡ ሰልጥነው ተመዝነው እንዲሰማሩ የሚያደርግ ነው ብለዋል።   በአዋጁ ጠንካራ የሆነ የስልጠናና የምዝና ስርዓት እንደ አንድ ጠንካራ ስርዓት ተደርጎ መካተቱን ሚኒስትሯ ተናግረዋል።     የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ አዋጁ ዜጎችን ከህገ ወጥ ደላሎች የሚታደግና የዜጎችን ክብርና ደህንነት የሚያስጠብቅ ነው ሲሉ ተናግረዋል።  
የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው
Jul 1, 2025 59
  አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ። አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ በስፔን ሲቪያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በኮንፍረንሱ እየተሳተፈ ነው። ሚኒስትሩ በኮንፍረንሱ ባደረጉት ንግግር ከ10 አመት በፊት በአዲስ አበባ ሶስተኛው ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይሁንና በኮንፍረንሱ የጸደቀው የአዲስ አበባ የድርጊት መርሃ-ግብር የአተገባበር ተግዳሮት እንደገጠመው ጠቅሰው የሲቪያ ስምምነት ይህንን ተግዳሮት የሚሻገር መሆን እንደሚገባው አመልክተዋል። ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመተግበር ከሚያስፈልገው ፋይናንስ ውስጥ የ4 ትሪሊዮን ዶላር እጥረት መግጠሙን አንስተዋል። ይህ ሁኔታ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራትን ለዘርፈ-ብዙ ተግዳሮቶች ዳርጓቸዋል ነው ያሉት ሚኒስትሩ። ለአብነትም አዳጊ ሀገራት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ ለሚመጡ ቀውሶች እና ለእዳ ጫና መጋለጣቸው አሳሳቢ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ኮርፖሬሽኖች ላይ ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ የታክስ ስርዓትን መተግበርና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጥላ ስር በየነ-መንግስታዊ የብድር አስተዳደርን በማቋቋም ዘላቂ ያልሆነ የብድር ችግሮችን መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል። በተጨማሪም የልማት ፋይናንስ ድጋፎችና ብድሮች ሀገራት ቅድሚያ ከሚሰጣቿው ጉዳዮችና እቅዶች ጋር መጣጣም እንዳለባቸውና አዳጊ ሀገራት የሚያገኙት የፋይናንስ ድጋፍ መጨመር እንዳለበት አመልክተዋል። በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ዘላቂ እና ተገማች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖራቸውና ቀውሶችን በተገቢው መንገድ ማስተዳደር እንዲችሉና ዓለም ዓቀፍ የልማት ፋይናንስ ስምምነቶች በተገቢው እንዲተገበሩ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ሊኖር እንደሚገባም ነው የገለጹት። በአፍሪካ እና በአጠቃላይ አዳጊ ሀገራት በመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ የስራ ዕድል ፈጠራና የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የሚያስችል የፋይናንስ አቅርቦት በአስተማማኝ መልኩ ማቅረብ ድህነትን ለመቀነስ እና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ሚኒስትሩ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን “ዓለም አቀፍ ትብብርን በአዲስ መልክ ማደስ” በሚል ርዕስ በሚኒስትሮች ደረጃ በተደረገው ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል። ሁለተኛው ቀኑን የያዘው አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ልዑክ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን እየተካሄዱ ባሉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል።
በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል
Jul 1, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞችን በሕግ ተጠያቂ ማድረጉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተካሂዷል። የወንጀል ምርመራ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊና የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሙስና፣ በህገ ወጥ የሰዎችና የጦር መሳሪያ ዝውውር፣ በኮንትሮባንድና አደንዛዥ ዕጽ ዝውውር የተጠረጠሩ ሰዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል በህግ ተጠያቂ መደረጋቸውን አስታውቀዋል። ኮሚሽኑ ሕግን ለማስከበር በወሰደው እርምጃ 1 ሺህ ተጠርጣሪዎች ላይ የተለያየ መጠን ያለው የቅጣት ውሳኔ መተላለፉን አንስተዋል። በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር የተሳተፉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ በማድረግና የምርመራ መዝገብ በማጠናቀቅ ለጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ቀርቦ ክስ እንዲመሰረትባቸው መደረጉን ተናግረዋል። እነዚህ ተጠርጣሪዎች ሀሰተኛ መታወቂያና በርካታ ሲም ካርዶችን በመጠቀም፣ ሆቴሎችና ማረፊያ ቤቶችን በመከራየት ዜጎችን በማጭበርበር ላይ ተሰማርተው የነበሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዚህም በድርጊቱ ላይ የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞች ላይ ምርመራ አድርጎ ክስ በመመስረት ወደ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ መደረጉንም አብራርተዋል። ከሀገር ውስጥና ከውጭ ኃይሎች ጋር በማበር በሽብር ወንጀል የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት እንዲሁም ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በመሆን ለሕግ የማቅረብ ሥራ መከናወኑንም አስረድተዋል። በዚህም ከ450 በላይ ተጠርጣሪዎች በሰነድና በሰው ማስረጃ በማጣራት ክስ እንዲመሰረትባቸው የተደረገ ሲሆን በህግ ተጠያቂ መሆናቸውንም ገልጸዋል። በኮንትሮባንድና ሕገ ወጥ ጦር መሳሪያ ዝውውር ላይ የተሳተፉ 143 ተጠርጣሪዎች ለሕግ መቅረባቸውን ጠቁመው ካናቢስ፣ ኮኬይንን ጨምሮ የተለያየ መጠን ያላቸው አደንዛዥ ዕጾች ዝውውር ወንጀል የተሳተፉ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ውለው ተጠያቂ ተደርገዋል ብለዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ በበጀት ዓመቱ ከ6 ሺህ በላይ የምርመራ መዝገቦች ምርመራ ተጠናቆ ለፍትህ ሚኒስቴር የተላከ ሲሆን በዚህም በሀገርና በህዝብ ላይ ጉዳት በማድረስ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። አቶ ሙሊሳ አክለውም በዘረ መል/DNA/ ምርመራ ዘርፍም ከ300 በላይ የምርመራ ጉዳዮች መቅረባቸውን አስታውሰው ወቅቱንና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ምርመራ ተከናውኖ የተገኘው ውጤት ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል። አጭበርባሪዎች ከባንክ የተደወለ በማስመሰል እያጭበረበሩ መሆኑን የገለጹት ሃለፊው ከባንክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም ዓይነት የባንክ አገልግሎት እንደሌለ ዜጎች ሊገነዘቡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ዜጎች የሚስጥር ቁጥራቸውን ለሶስተኛ ወገን አሳልፈው መስጠት የለባቸውም ያሉት አቶ ሙሊሳ ህብረተሰቡ የአጭበርባሪዎች ሰለባ እንዳይሆን ሊጠነቀቅ እንደሚገባ አመልክተዋል።
በክልሉ ለህዝቡ የልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለአገልግሎት የማብቃቱ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል-አቶ አወሉ አብዲ
Jul 1, 2025 62
አምቦ ፤ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፦ በክልሉ ለህዝቡ የልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለአገልግሎት የማብቃቱ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አወሉ አብዲ ገለጹ። ምክትል ፕሬዝዳንቱ በአምቦ ከተማ ግንባታቸው የተጠናቀቁ 25 የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግርም በክልሉ የህዝብን የልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለአገልግሎት የማብቃቱ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   በአምቦ ከተማ የተገነቡት ፕሮጀክቶችም የዚሁ ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰው ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት የመገንባት ስራ በልዩ ትኩረት ይከናወናል ብለዋል። የአምቦ ከተማ ከንቲባ ሃጫሉ ገመቹ፤ የከተማዋን ነዋሪዎች የረጅም ጊዜ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት በዛሬው እለት ለህዝብ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸው 25 የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን ተናግረዋል።   የፕሮጀክቶቹ ወጪም በመንግስት፣ በህብረተሰብ ተሳትፎና በአጋር ድርጅቶች የተሸፈነ መሆኑን ጠቅሰው መሰል ስራዎች በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላሉ ብለዋል። በዛሬው እለት ለምርቃት ከበቁት ፕሮጀክቶች መካከል የእንስሳት ማደለቢያ፣ የወተት ላሞች እርባታ እና የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ፣ ትምህርት ቤት እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡   የፕሮጀክቶቹ መመረቅ በአጠቃላይ ለከተማውና ለአካባቢው ነዋሪ ፋይዳቸው የላቀ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።  
በሌማት ትሩፋት እየተገኘ ያለው ውጤት እየጨመረ ነው - ግብርና ሚኒስቴር
Jul 1, 2025 59
  አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሌማት ትሩፋት መርኃ-ግብር እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት በየአመቱ እየተገኘ ያለው ውጤት እየጨመረ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሌማት ትሩፋት መርሐ ግብርን ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ ማስጀመራቸው ይታወሳል። የሌማት ትሩፋት መርኃ-ግብር ከተጀመረ 3 አመታት የተቆጠረ ሲሆን በዚህም በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት በሀገሪቱ ከዛሬ ሶስት አመት በፊት የተጀመረው የሌማት ትሩፋት በርካታ አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡበት ነው፡፡ በተለይ መርሃ ግብሩ ከተጀመረ ግዜ ጀምሮ በሀገሪቱ የወተት፣ የዶሮ ሥጋ፣ እንቁላል፣ የማርና ዓሳ ምርት እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰዋል። በመንግስት የተሰጠው ትኩረት ባሻገር ከፍተኛ የህዝብ ፍላጎት፣ የባለሃብቶች ተሳትፎ እያደገ መምጣቱ በየአመቱ በዘርፉ የሚገኘው ውጤት እንዲያድግ ምክንያት መሆኑን አስታውቀዋል።   በበጀት አመቱ 11 ወራት ብቻ በወተት በእንቁላል በሌሎች የእንስሳትና እንስሳት ተዋፅኦ ምርቶች ላይ የተገኘው ውጤት ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ብልጫ እንደታየበት ለአብነት አንስተዋል፡፡ በበጀት አመቱ አስራ አንድ ወራት 3 ነጥብ 8 ሚሊዮን እንስሳት ማዳቀል፣ 11 ነጥብ 4 ቢሊየን ሊትር ወተት፣ 7 ነጥብ 4 ቢሊዮን እንቁላል ማምረት መቻሉን ተናግረዋል። ሚኒስትር ዴኤታው በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ህብረተሰቡ ከውሃ አካላትና ከኩሬዎች በተጨማሪ በየአካባቢው፣ በጓሮው፣ በአነስተኛ ቦታ ዓሳ እንዲያመርት ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ እንደሆነም ተናግረዋል።   በባህርዳር፣ በባቱ፣ በአርባ ምንጭ፣ በሐዋሳ እና በሰበታ የሚገኙ ዓሳ ጫጩት ማስፈልፈያ ማዕከላትን የማጠናከር ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።   ባለፉት ሶስት አመታት በተሰራው ስራ የአሳ ምርት አቅርቦት እያደገ ሲሆን ባለፉት 11 ወራት ብቻ 253ሺህ ቶን የዓሳ፣ 190 ሺህ ቶን የዶሮ ስጋ እንዲሁም 296ሺህ ቶን የማር ምርት መገኘቱን ተናግረዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል
Jul 1, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞችን በሕግ ተጠያቂ ማድረጉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተካሂዷል። የወንጀል ምርመራ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊና የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሙስና፣ በህገ ወጥ የሰዎችና የጦር መሳሪያ ዝውውር፣ በኮንትሮባንድና አደንዛዥ ዕጽ ዝውውር የተጠረጠሩ ሰዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል በህግ ተጠያቂ መደረጋቸውን አስታውቀዋል። ኮሚሽኑ ሕግን ለማስከበር በወሰደው እርምጃ 1 ሺህ ተጠርጣሪዎች ላይ የተለያየ መጠን ያለው የቅጣት ውሳኔ መተላለፉን አንስተዋል። በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር የተሳተፉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ በማድረግና የምርመራ መዝገብ በማጠናቀቅ ለጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ቀርቦ ክስ እንዲመሰረትባቸው መደረጉን ተናግረዋል። እነዚህ ተጠርጣሪዎች ሀሰተኛ መታወቂያና በርካታ ሲም ካርዶችን በመጠቀም፣ ሆቴሎችና ማረፊያ ቤቶችን በመከራየት ዜጎችን በማጭበርበር ላይ ተሰማርተው የነበሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዚህም በድርጊቱ ላይ የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞች ላይ ምርመራ አድርጎ ክስ በመመስረት ወደ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ መደረጉንም አብራርተዋል። ከሀገር ውስጥና ከውጭ ኃይሎች ጋር በማበር በሽብር ወንጀል የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት እንዲሁም ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በመሆን ለሕግ የማቅረብ ሥራ መከናወኑንም አስረድተዋል። በዚህም ከ450 በላይ ተጠርጣሪዎች በሰነድና በሰው ማስረጃ በማጣራት ክስ እንዲመሰረትባቸው የተደረገ ሲሆን በህግ ተጠያቂ መሆናቸውንም ገልጸዋል። በኮንትሮባንድና ሕገ ወጥ ጦር መሳሪያ ዝውውር ላይ የተሳተፉ 143 ተጠርጣሪዎች ለሕግ መቅረባቸውን ጠቁመው ካናቢስ፣ ኮኬይንን ጨምሮ የተለያየ መጠን ያላቸው አደንዛዥ ዕጾች ዝውውር ወንጀል የተሳተፉ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ውለው ተጠያቂ ተደርገዋል ብለዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ በበጀት ዓመቱ ከ6 ሺህ በላይ የምርመራ መዝገቦች ምርመራ ተጠናቆ ለፍትህ ሚኒስቴር የተላከ ሲሆን በዚህም በሀገርና በህዝብ ላይ ጉዳት በማድረስ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። አቶ ሙሊሳ አክለውም በዘረ መል/DNA/ ምርመራ ዘርፍም ከ300 በላይ የምርመራ ጉዳዮች መቅረባቸውን አስታውሰው ወቅቱንና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ምርመራ ተከናውኖ የተገኘው ውጤት ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል። አጭበርባሪዎች ከባንክ የተደወለ በማስመሰል እያጭበረበሩ መሆኑን የገለጹት ሃለፊው ከባንክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም ዓይነት የባንክ አገልግሎት እንደሌለ ዜጎች ሊገነዘቡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ዜጎች የሚስጥር ቁጥራቸውን ለሶስተኛ ወገን አሳልፈው መስጠት የለባቸውም ያሉት አቶ ሙሊሳ ህብረተሰቡ የአጭበርባሪዎች ሰለባ እንዳይሆን ሊጠነቀቅ እንደሚገባ አመልክተዋል።
ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶችን ማስቀጠል ይገባል - አቶ አደም ፋራህ
Jul 1, 2025 86
ወላይታ ሶዶ ፤ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፡-የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። ''ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሄዷል።   በወቅቱም አቶ አደም ፋራህ እንዳሉት፤ በክልሉ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች እየተመዘገበ ያለውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል ተደጋግፎ መስራት ይገባል። ኮንፈረንሱ በክልሉ ሰላም፣ ልማትና አንድነት ላይ አዎንታዊ ለውጥ በማምጣትና የህዝቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል። በቀጣይ ጊዜያት ከፋፋይ ትርክቶችን በማስወገድ በመደመር ዕሳቤ ወንድማማችነት እና እህትማማችነትን አጠናክሮ በማስቀጠል የብልጽግና ጉዞን ማፋጠን ያስፈልጋል ብለዋል። የጋራ ማንነትን የሚያጎለብቱ ህብረ-ብሔራዊነትን ለማረጋገጥ ያለፈውን ቅሬታ በይቅርታ አልፎ ለወደፊት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ጠንካራ ክልላዊ ተቋማትን ፈጥሮ በብቁ አመራር እንዲመሩ በማድረግ ብልሹ አሰራርን እና ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ መፍጠር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። የተለያዩ የልማት ኢኒሼቲቮችን ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የክልሉን ብልጽግና ለማረጋገጥ መትጋት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ከክልሉ ምስረታ ማግስት ጀምሮ አብሮነትን የሚያጸኑ የጋራ ትርክቶችን ለማስረጽ የተሰራው ስራ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። ክልሉ ካለው የመልማት አቅም አንፃር ያልተሻገርናቸው በርካታ ነገሮች አሉ ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በሁሉም መስክ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መትጋት እንደሚገባ አሳስበዋል። ''ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ ሲካሄድ የቆየው ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ ዛሬ ተጠናቋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የሦስት አገራት አምባሳደሮችን አሰናበቱ
Jun 30, 2025 195
አዲስ አበባ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በኢትዮጵያ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የካናዳ፣የስዊዲንና የሳኡዲ አረቢያ አምባሳደሮችን አሰናበቱ። ፕሬዝዳንቱ ያሰናበቱት የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ፣የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክና የሳኢዲ አረቢያ አምባሳደር ፋሃድ አልሁማያዳኒ (ዶ/ር) ናቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ ሦስቱም አምባሳደሮቹ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከአገራቱ ጋር በተለያዩ መስኮች የሁለትዮሽ ግንኙነትና ትብብር እንዲጠናከር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።   በተለይም የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲሳለጥ እንዲሁም በሌሎች የልማት የትብብር ዘርፎች ግንኙነቱ እንዲጠናከር ላደረጉት አስተዋጽዖም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አምባሳደሮቹ በሌሎች መስኮች ለአብነትም በመልሶ ማልማት ሥራዎች ጉልህ አስተዋጽኦ መደረጉን አንስተው፥ትብብሮች በቀጣይም ሊጠናከር እንደሚገባ ጠይቀዋል። በቀጣይ በተለይም ውጤታማ የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቶች ይበልጥ ሊጠናከሩ እንደሚገባ ጥሪ ማቅረባቸውን ውይይቱን የተከታተሉት የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አምባሳደር ትዝታ ሙሉጌታ ለኢዜአ ገልጸዋል። አምባሳደሮቹ በበኩላቸው፥ በኢትዮጵያ ቆይታቸው አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር በርካታ ሥራዎች መሥራታቸውንና በዚህም አመርቂ ውጤት መገኙቱን ጠቅሰዋል። የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ በቆይታቸው የካናዳና ኢትዮጵያን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማስፋት የሚያስችሉ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል።   በተመሳሳይ የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ በቆይታቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ቅድሚያ በሰጠባቸው መስኮች ትብብር በማድረግ አበረታች ሥራዎች ማከናወናቸውን አስረድተዋል። አምባሳደሮቹ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች እየተዘመገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውንና መሰል ሥራዎችን ሊያጠናክር እንደሚገባ ተናግረዋል። በቀጣይም ግንኙነቱ ይበልጥ እንዲጠናከር የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
በቀበሌ ደረጃ መንግስታዊ አገልግሎት ተደራሽ መደረጉ ቀልጣፋ አገልግሎት ከማስገኘቱ ባለፈ የልማት ተሳታፊነታችንን እያሳደገ ነው -ነዋሪዎች
Jun 30, 2025 104
ጭሮ ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በቀበሌ ደረጃ መንግስታዊ አገልግሎት ተደራሽ በመደረጉ ለአስተዳደራዊ ጉዳዮቻቸው ፈጣን ምላሽ ከማስገኘቱ ባለፈ የልማት ተሳታፊነታቸው እያደገ መምጣቱን የዞኑ ዶባ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። በዞኑ በአዲስ መልክ ለተዘረጋው የቀበሌ አስተዳደር አገልግሎት መስጫ የሚውሉ ጽህፈት ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ ነው። ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት ለህብረተሰቡ ቅርብ የሆኑ የቀበሌ መዋቅሮች ከዚህ ቀደም ትኩረት በማጣታቸው አገልግሎት ፍለጋ እስከ ወረዳ ማዕከላት ሲመላለሱ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት የቀበሌ ፅህፈት ቤቶች በዘመናዊ መልኩ ተገንብተው ሙሉ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን የተናገሩት በወረዳው የባቱ ቀበሌ ነዋሪ ኢብራሂም ሁሴን ናቸው።   በጤና፣ በትምህርት፣ በግብርና እና መሰል ጉዳዮች አገልግሎት ፍለጋ እስከ ወረዳ ማዕከል ድረስ ሲመላለሱ እንደነበር ያነሱት አስተያየት ሰጪው አሁን ላይ እነዚህን አገልግሎቶች በአካባቢያቸው በሚገኝ ቀበሌ ጽህፈት ቤት በቅርበት አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል። ከዚህ ቀደም በወረዳ ደረጃ ብቻ የሚያገኙትን የመሬት ነክ እና ግብርና አገልግሎቶችን በቀበሌ ማግኘታቸው የልማት ተሳታፊነታቸውን እያሳደገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አህመድ ኢብሮ ናቸው። ይህም የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን በማቃለል በአካባቢያቸው በሚከናወኑ የልማት ስራዎች ውስጥ ተሳትፏቸው እንዲጨምር ማድረጉንም ተናግረዋል። በብልጽግና ፓርቲ የዶባ ወረዳ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሙዘይን ከማል እንዳሉት በወረዳው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ በተጀመረው የቀበሌ አገልግሎት ማጠናከር ስራ ህብረተሰቡ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረግ ተችሏል። ሙሉ አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ በቅርበት እንዲሰጡ በመደረጉም አርሶ አደሩ ከግብርና ስራው እንዳይስተጓጎል ሁሉንም መንግስታዊ አገልግሎት በቅርበት እንዲያገኝ ማድረጉን ተናግረዋል። በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በሚገኙ 15 ወረዳዎችና አምስት ከተሞች የቀበሌ አደረጃጀቶችን በማጠናከር 3 ሺህ 522 ባለሙያዎች ተመድበው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ኢክራም ጠሀ ናቸው።   በዚህም 512 የቀበሌ ፅህፈት ቤቶች በዘመናዊ መልኩ እንዲገነቡ መደረጉን አመልክተዋል።  
መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደ ትናንቱ በትጋት ይሠራል - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Jun 29, 2025 218
  አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደ ትናንቱ በትጋት እንደሚሰራ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የአማራ ክልል ሕዝብ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መክፈል የማይገባውን ውድ ዋጋ በጥቂት ጥቅመኞች ምክንያት እየከፈለ መሆኑን ገልጿል። የፋኖን ታሪካዊ አነሣሥና ዓላማ ባልተከተለ አግባብ ራሳቸውን በፋኖ ስም የሚጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች በቀሰቀሱት ግጭትም የአማራ ክልል ሰላም እና ልማት ክፉኛ መጎዳቱን ጠቁሟል። መንግሥት ባለፉት ዓመታት ግጭቶችን ለማስወገድ በርካታ አማራጮችን ሲከተል መቆየቱ የሚታወስ ነው ያለው አገልግሎቱ ጥያቄ ያላቸዉ አካላትን በማቅረብ ለማነጋገር እና ለመደራደር በርካታ ጥረቶችን ማድረጉን ገልጿል ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- የአማራ ክልል ሕዝብ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መክፈል የማይገባዉን ውድ ዋጋ በጥቂት ጥቅመኞች ምክንያት እየከፈለ ይገኛል፡፡ የፋኖን ታሪካዊ አነሣሥ እና ዓላማ ባልተከተለ አግባብ ራሳቸዉን በፋኖ ስም የሚጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች በቀሰቀሱት ግጭት የአማራ ክልል ሰላም እና ልማት ክፉኛ ተጎድቷል፡፡ ፋኖ ሀገር በባዕድ ወራሪ እጅ በወደቀችበት እና ማእከላዊ መንግሥት በግዞት በቆየበት ወቅት ሀገርን ለማዳን የተደረገ ተጋድሎ የተመራበት ድንቅ ስያሜ ነው፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ግን የሀገሩን እና የክልሉን መንግሥት ለማፍረስ እና የባዕዳንን ተልእኮ ለማሳካት የተደራጁ ቡድኖች መጠሪያ ተደርጎ ሀገርን እና ሕዝብን ውድ ዋጋ አስከፍሏል፡፡ በሚሊዮኖች የሚቈጠሩ ታዳጊዎችን ከትምህርት ገበታ ነጥሏል፡፡ ሕዝብን ከልማት እንቅስቃሴዎች አሰናክሏል። የአማራ ክልል ሕዝብም የግጭት ጠማቂዎቹን እና የተላላኪዎቹን አጀንዳ በሚገባ ተገንዝቦ መንግሥት ሰላም እንዲያሰፍን በተደጋጋሚ ጥያቄዎችን በተለያዩ አግባቦች ሲያቀርብ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ የአማራ ክልል ሕዝብ ክልሉን ከግጭት እና ሥርዐት አልበኝነት ለማውጣት በየአካባቢዉ ተሰባስቦ ምክክር እና ውይይት አካሂዷል። የክልሉ ሕዝብ ጥያቄዎች በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን በአጀንዳነት እንዲያዙ አድርጓል፤ ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራዉ ቡድን ትክክለኛ የነፃነት ታጋይ መስሎት የተቀላቀለ ወጣት ወደ ሰላማዊ ሕይወቱ እንዲመለስ በሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ለምኗል፡፡ ከዚህም መሳ ለመሳ የፌደራል የፀጥታ ተቋማት እና የክልሉ የፀጥታ መዋቅር የክልሉን ሰላም ለማረጋጥ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፤ መሥዋዕትነትም ከፍለዋል፤ እየከፈሉም ነው፡፡ በዚህም በክልሉ አብዛኞቹ አካባቢዎች ሰላም ማስፈን ተችሏል፡፡ በተፈጠረው አስቻይ ሁኔታም የክልሉ ሕዝብ ከልማት ጥረቶች ወደ ኋላ እንዳይቀር በርካታ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል። ይሁን እንጅ በፀጥታ ኃይላችን ጥረት እና በሀገር ሽማግሌዎች ተማፅኖ አንጻራዊ ሰላም ቢሰፍንም ሕዝቡ በሚሻዉ ልክ የክልሉ ሰላም ሙሉ ለሙሉ አልተረጋገጠም፤ የዜጎች እንቅስቃሴ ከእገታና ዘረፋ ስጋት በምልዓት አልተላቀቀም፡፡ የነገ ሀገር ተረካቢዎች በተሟላ መልኩ ወደ ትምህርት ገበታ አልተመለሱም፡፡ የልማት እንቅስቀሴዎች ሕዝብ እና መንግሥት በሚሹት ልክ እንዲፋጠኑ ምቹ ድባብ አልሰፈነም፡፡ በዚህ ምክንያት ሕዝቡ ብሶቱን ለመንግሥት ጎላ አድርጎ ለማሰማት በተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን አካሂዷል፡፡ በሰላማዊ ሰልፎቹ መንግሥት የክልሉን ሰላም በማረጋገጥ ልማትን እንዲያጠናክር ሕዝቡ ጠይቋል፡፡ መንግሥት የውስጥ ባንዳዎችን እና የውጭ ኃይሎችን አደብ እንዲያስገዛለት፣ ልጆቹ ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱለት፣ ማሳውን ወደ መጎልጎልና ማረስ እንዲሰማራ፣ በኑሮው በሰላም ወጥቶ መግባት እንዲችል ምቹ ድባብ እንዲፈጠርለት፣ ሰላሙን በጋራ ለመጠበቅ እንደተዘጋጀ እና መንግሥት ሕግ ለማስከበር የጀመረዉን ጥረት በፅናት እንደሚደግፍ በሰላማዊ ሰልፎቹ ገልጿል፡፡ መንግሥት ባለፉት ዓመታት ግጭቶችን ለማስወገድ በርካታ አማራጮችን ሲከተል መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ ጥያቄ ያላቸዉ አካላትን በማቅረብ ለማነጋገር እና ለመደራደር በርካታ ጥረቶችን አድርጓል፡፡ በተደጋጋሚ የይቅርታ እና ምሕረት ጥሪዎችን አቅርቧል፡፡ በዚህም በርካታ በስሕተት የጥፋት ኃይሎችን ተቀላቅለዉ የነበሩ አካላት እጃቸዉን በመስጠት ሕይወታቸዉን አትርፈዋል፤ ሕዝቡን ለመካስ የሚያስችል የተሐድሶ ሥልጠናም አግኝተዋል፡፡ ነገር ግን አሁንም ጥቂት ጥቅመኞች የሕዝቡን ሰላም እያወኩ የባዕዳንን ተልእኮ ለማሳካት እየተወራጩ ይገኛሉ፡፡ መንግሥት የሕዝቡን የሰላም፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደትናንቱ ዝግጁ ነው፤ መንግሥታዊ ኃላፊነቱም ነው፡፡ የአማራ ክልል ሕዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ ከክልሉ ሕዝብ፣ ከክልሉ አስተዳደር እና የፀጥታ ኃይል ጋር በመቀናጀት መንግሥት የላቀ ጥረት ያደርጋል፡፡ ሕዝቡ ከመንግሥት ጋር በመቀናጀት ሰላሙን ለመጠበቅ ያሳየዉን ቁርጠኝነትም ያደንቃል፡፡ የሰላም በሮችን ዛሬም ክፍት አድርጎ እየጠበቀ የሕዝቡን የሰላም እና የልማት ጥያቄ ለመመለስ ከመቼዉም ጊዜ በላቀ ደረጃ ዝግጁ መኾኑንም መንግሥት ያረጋግጣል፡፡ የሰላም አማራጮችን የማይቀበሉ አካላትን በክልሉ የፀጥታ መዋቅር እና በፌደራል መዋቅር አማካኝነት አደብ በማስገዛት የሕዝቡን ሰላም ለማረጋገጥ ይሠራል፡፡ ሕዝቡ በአደባባይ ያቀረባቸዉን ጥያቄዎች ከሕዝብ ጋር ለመመለስ ያላሰለሰ ጥረት ያደርጋል፡፡ ሕዝቡ በሠለጠነ አግባብ ሐሳቡን በመግለጹም መንግሥት ምስጋና ያቀርባል፡፡ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
መንግስት ህግ በማስከበር ሰላምና ልማትን ለማጽናት እያደረገ ላለው ጥረት ተሳትፏችንን እናጠናክራለን
Jun 29, 2025 151
ደብረ ብርሃን፣ደብረ ማርቆስ፣ገንዳ ውሃና ወልዲያ፤ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦መንግስት ህግ በማስከበር ሰላምና ልማትን ለማጽናት እያደረገ ላለው ጥረት ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎች ገለጹ። በክልሉ ደብረ ብርሃን፣ደብረ ማርቆስ፣ መተማ ዮሐንስ እና ወልዲያ ከተሞች ሰላምን የሚደግፉና ጽንፈኝነትን የሚያወግዙ ህዝባዊ ሰልፎች ዛሬ ተካሂደዋል። በደብረ ብርሃን ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ሰልፍ የተሳተፉት አቶ ከፍያለው ግርማ በሰጡት አስተያየት የሰላም እጦት ችግር በውይይትና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ታጥቀው በጫካ ያሉ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ወደሰላም እንዲመጡና የሰላም ፍላጎታቸውን ለማሰማት በሰልፉ መታደማቸውን ተናግረዋል።   ኑሮውን ሎተሪ አዙሮ በመሸጥ የሚመራው ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ በፍቃዱ በለጠ በበኩሉ፥ሰርቶ ለማደግና ለመለወጥ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ገልጾ፣ ሰላም እንደሚፈልግ በጋራ ድምጹን ለማሰማት በሰልፉ መሳተፉን ገልጿል። የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የሰላም እጦት ችግሩን ለመፍታት መንግስት ህግ ከማስከበር ጎን ለጎን ለታጠቁ አካላት በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ማቅረቡን አስታውሰዋል።   የጥፋት ሀይሎች በህዝብና በሀገር ላይ እየፈጸሙት ያለውን የጥፋት ተግባር በማቆም የህዝብን ጽኑ የሰላም ፍላጎት በማክበር የመንግስትን የሰላም አማራጭ ሊቀበሉ ይገባል ብለዋል። በተያያዘ ዜና በደብረ ማረቆስ ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ሰልፍ ላይ የተሳተፉት ወይዘሮ እታገኝ አዳነ፥ ባለፉት ሁለት ዓመታት ያሳለፍነው ችግር እንዲያበቃ እንፈልጋለን፤ የእኛ ፍላጎት ዘላቂ ሰላምና ልማት ነው ብለዋል። ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም እንዲመጡ እንፈልጋለን ያሉት ወይዘሮ እታገኝ፣ ለአካባቢው ሰላም መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።   ሌላዋ ተሳታፊ ወይዘሮ አንለይ ተረፈ በበኩላቸው፥ ሰው በሰላም ወጥቶ መግባትና ሰርቶ መብላት የሚችለው ሰላም ሲኖር ነው ብለዋል።   ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ በላይ እንየው በበኩላቸው፥ በግጭት ሰቆቃ፣ መከራና ስቃይ እንጂ የሚመጣ ለውጥ የለም ፤ ሰላምን እንደምንፈልግ በይፋ ለመግለጽ ዛሬ በሰልፉ ላይ ተገኝተናል ብሏል። አንድነታችንን በማጠናከር ሰላምና ልማትን ማጽናት የትኩረት አቅጣጫችን ነው ያሉት ደግሞ የደብረ ማርቆስ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ ናቸው። "ህዝቡ ለሰላሙ ያሳየውን ቁርጠኝነት በማስቀጠል በከተማው የተጀመረው የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ፣የኮሪደር ልማትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እናበቃለን ብለዋል። የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ በበኩላቸው፥ ህብረተሰቡ በተባበረ ድምጽ ጽንፈኞች ከጥፋት ተግባራቸው እንዲታቀቡ ያሳየው ቁርጠኝነት ትልቅ አቅም ነው ብለዋል። በሌላ በኩል በመተማ ዮሐንስ ከተማ በተካሄደ ሰልፍ የተሳተፉት አቶ ጥላሁን ንጉሴ በበኩላቸው፥በአካባቢው ጸጥታ ችግር ምክንያት ህዝቡ በሰላም ወጥቶ መግባት ቀርቶ የተሻለ ህክምና እንኳ ለማግኘት ተቸግሮ እንደነበር አስታውሰዋል። መንግስት የጀመረውን የህግ የማስከበር ሥራ እንደሚደግፉ ገልጸው፣ በጫካ ያለው ሃይል የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበልና ሰላምን እንደምንፈልግ መልዕክት ለማስተላለፋ ሰልፍ መውጣታቸውን ተናግረዋል። ሌላኛዋ የሰልፉ ተሳታፊ ወይዘሮ ሲሳይነሽ ይርጋ በበኩላቸው፥ ፅንፈኝነት የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን ጭምር ሰለባ እያደረገ በመሆኑ ከመንግስት ጎን ሆነው ለመታገል ቁርጠኛ መሆናቸውን ነው የገለጹት። ጽንፈኝነትን ማውገዝ ብቻ ሳይሆን መታገልም ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የመተማ ዮሐንስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሀብቴ አዲሱ ናቸው። መንግስት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ልማትን ለማረጋገጥ የጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ህዝቡ ከመንግስት ጎን ሆኖ የሚያደርገውን አስተዋጾ እንዲያጠናክርም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ በወልዲያ ከተማ በተካሄደ ሰልፍ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሰላም እጦት ያተረፉት የሰዎች ሞት፣ እገታ፣ ዝርፊያና ስደትን ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። መንግስት ሰላም እንዲጠናከር ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች ወደሰላም እንዲመጡ ያቀረበውን ጥሪ እንደሚደግፉ ገልጸው፣ የጥፋት ሀይሎች ጥሪውን በመቀበል ወደሰላም እንዲመጡ ጠይቀዋል። የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፥የጽንፈኞች እኩይ ሴራ የልማት ሥራን እንዳያደናቅፍ ጠንክሮ መታገል ይገባል ብለዋል። የታጠቁ ሃይሎችም የህዝብን ድምጽ በመስማትና በማክበር መንግስት በተደጋጋሚ ያቀረበውን የሰላም አማረጭ ተቀብለው ህዝባቸውን እንዲክሱም ከንቲባው አስገንዝበዋል። በተለያዩ ከተሞች በተካሄዱ ህዝባዊ ሰልፎች ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለሰላም ጽኑ ፍላጎት እንዳላቸውና ጽንፈኝነት ሀገርና ህዝብን ስለሚጎዳ ለሰላማቸው ከመንግስት ጎን እንደሚቆሙ ገልጸዋል።
ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እና ልማት እንዲፋጠን ድጋፋችንን እናጠናክራለን
Jun 29, 2025 165
ባህርዳር፤ ሰኔ 22/2017 (ኢዜአ) በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እና የልማት ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በባህርዳር ከተማ የህዝባዊ ሰልፍ ተሳታፊዎች ገለጹ። በባህርዳር ከተማ ‘‘ሀገርን ለማፅናት እና ለማበልፀግ ከመንግስት ጎን እንሰለፋለን’’ በሚል መሪ ሀሳብ ሰላምን የሚደግፍ ህዝባዊ ሰልፍ ዛሬ ተካሂዷል። ከሰልፉ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ትዕዛዙ ገብረኢየሱስ ለኢዜአ እንደገለጸው በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ ለህዝቡ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው።   በክልሉ አሁን ላይ ባለው ሰላም በከተማው ልማት እንዲፋጠንና የወጣቶች ተጠቃሚነት እያደገ እንዲመጣ ማስቻሉን ገልጿል። የተገኘው ሰላም ዘላቂ እንዲሆንና የልማት ስራዎች እንዲጠናከሩ ተሳትፏችንን እናጠናክራለን " ያለው ወጣት ትዕዛዙ የታጠቁ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም እንዲመጡ ጠይቋል ። "የሰላም እጦት የሚያስከትለው ጥፋት በመሆኑ ለሰላም ዘብ ለመቆም ቆርጠን ተነስተናል" ያሉት ደግሞ የሰልፉ ታዳሚ ወይዘሮ አስረሱ ጌትነት ናቸው። በከተማው አሁን ላይ ባለው ሰላም ተስፋ ሰጭ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን ተናግረዋል።   "በጫካ ላሉ የታጠቁ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላም ሊመጡ ይገባል" ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል። ‘‘በክልላችን ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ ድምፃችንን ለማሰማት በሰልፉ ተሳትፈናል ’’ ያለው ደግሞ ወጣት ሳለአምላክ አድማሱ ነው። ሰላም ለአንድ ወገን የሚተው አለመሆኑን ጠቁሞ "ሁላችንም ከመንግስት ጎን በመሰለፍ ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ልማት እንዲረጋገጥ በቁርጠኝነት ልንሰራ ይገባል" ብሏል።   የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው የከተማው አስተዳደር ሰላምን በማጽናት ልማትን ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። "ፅንፈኛው ኃይል በክልሉና በከተማችን ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት አድርሷል" ያሉት አቶ ጎሹ ህፃናት ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ ማድረጉን ጠቅሰዋል። የፅንፈኛው ሀይል የክልሉን ልማትና ዕድገት ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ህብረተሰቡ በዛሬው ሰልፍ ጽንፈኝነትን በማውገዝ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የደገፈበት መሆኑን ተናግረዋል ።   ጫካ የሚገኙ ኃይሎች የሰላም ጥሪን ተቀብለው ህዝባቸውን እንዲክሱም አሳስበዋል። በከተማው ሰላምን ዘላቂ ለማድረግና ልማትን ለማፋጠን እየተደረገ ባለው ጥረት የህብረተሰቡ ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ይኽው የህዝቡ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል ። በሰልፉ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ፖለቲካ
በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል
Jul 1, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞችን በሕግ ተጠያቂ ማድረጉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተካሂዷል። የወንጀል ምርመራ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊና የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሙስና፣ በህገ ወጥ የሰዎችና የጦር መሳሪያ ዝውውር፣ በኮንትሮባንድና አደንዛዥ ዕጽ ዝውውር የተጠረጠሩ ሰዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል በህግ ተጠያቂ መደረጋቸውን አስታውቀዋል። ኮሚሽኑ ሕግን ለማስከበር በወሰደው እርምጃ 1 ሺህ ተጠርጣሪዎች ላይ የተለያየ መጠን ያለው የቅጣት ውሳኔ መተላለፉን አንስተዋል። በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር የተሳተፉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ በማድረግና የምርመራ መዝገብ በማጠናቀቅ ለጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ቀርቦ ክስ እንዲመሰረትባቸው መደረጉን ተናግረዋል። እነዚህ ተጠርጣሪዎች ሀሰተኛ መታወቂያና በርካታ ሲም ካርዶችን በመጠቀም፣ ሆቴሎችና ማረፊያ ቤቶችን በመከራየት ዜጎችን በማጭበርበር ላይ ተሰማርተው የነበሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዚህም በድርጊቱ ላይ የተሳተፉ ከ80 በላይ ዋነኛ ወንጀለኞች ላይ ምርመራ አድርጎ ክስ በመመስረት ወደ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ መደረጉንም አብራርተዋል። ከሀገር ውስጥና ከውጭ ኃይሎች ጋር በማበር በሽብር ወንጀል የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት እንዲሁም ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በመሆን ለሕግ የማቅረብ ሥራ መከናወኑንም አስረድተዋል። በዚህም ከ450 በላይ ተጠርጣሪዎች በሰነድና በሰው ማስረጃ በማጣራት ክስ እንዲመሰረትባቸው የተደረገ ሲሆን በህግ ተጠያቂ መሆናቸውንም ገልጸዋል። በኮንትሮባንድና ሕገ ወጥ ጦር መሳሪያ ዝውውር ላይ የተሳተፉ 143 ተጠርጣሪዎች ለሕግ መቅረባቸውን ጠቁመው ካናቢስ፣ ኮኬይንን ጨምሮ የተለያየ መጠን ያላቸው አደንዛዥ ዕጾች ዝውውር ወንጀል የተሳተፉ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ውለው ተጠያቂ ተደርገዋል ብለዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ በበጀት ዓመቱ ከ6 ሺህ በላይ የምርመራ መዝገቦች ምርመራ ተጠናቆ ለፍትህ ሚኒስቴር የተላከ ሲሆን በዚህም በሀገርና በህዝብ ላይ ጉዳት በማድረስ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። አቶ ሙሊሳ አክለውም በዘረ መል/DNA/ ምርመራ ዘርፍም ከ300 በላይ የምርመራ ጉዳዮች መቅረባቸውን አስታውሰው ወቅቱንና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ምርመራ ተከናውኖ የተገኘው ውጤት ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል። አጭበርባሪዎች ከባንክ የተደወለ በማስመሰል እያጭበረበሩ መሆኑን የገለጹት ሃለፊው ከባንክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም ዓይነት የባንክ አገልግሎት እንደሌለ ዜጎች ሊገነዘቡ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ዜጎች የሚስጥር ቁጥራቸውን ለሶስተኛ ወገን አሳልፈው መስጠት የለባቸውም ያሉት አቶ ሙሊሳ ህብረተሰቡ የአጭበርባሪዎች ሰለባ እንዳይሆን ሊጠነቀቅ እንደሚገባ አመልክተዋል።
ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶችን ማስቀጠል ይገባል - አቶ አደም ፋራህ
Jul 1, 2025 86
ወላይታ ሶዶ ፤ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፡-የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። ''ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሄዷል።   በወቅቱም አቶ አደም ፋራህ እንዳሉት፤ በክልሉ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች እየተመዘገበ ያለውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል ተደጋግፎ መስራት ይገባል። ኮንፈረንሱ በክልሉ ሰላም፣ ልማትና አንድነት ላይ አዎንታዊ ለውጥ በማምጣትና የህዝቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል። በቀጣይ ጊዜያት ከፋፋይ ትርክቶችን በማስወገድ በመደመር ዕሳቤ ወንድማማችነት እና እህትማማችነትን አጠናክሮ በማስቀጠል የብልጽግና ጉዞን ማፋጠን ያስፈልጋል ብለዋል። የጋራ ማንነትን የሚያጎለብቱ ህብረ-ብሔራዊነትን ለማረጋገጥ ያለፈውን ቅሬታ በይቅርታ አልፎ ለወደፊት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ጠንካራ ክልላዊ ተቋማትን ፈጥሮ በብቁ አመራር እንዲመሩ በማድረግ ብልሹ አሰራርን እና ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ መፍጠር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። የተለያዩ የልማት ኢኒሼቲቮችን ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የክልሉን ብልጽግና ለማረጋገጥ መትጋት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ከክልሉ ምስረታ ማግስት ጀምሮ አብሮነትን የሚያጸኑ የጋራ ትርክቶችን ለማስረጽ የተሰራው ስራ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። ክልሉ ካለው የመልማት አቅም አንፃር ያልተሻገርናቸው በርካታ ነገሮች አሉ ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በሁሉም መስክ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መትጋት እንደሚገባ አሳስበዋል። ''ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ ሲካሄድ የቆየው ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ ዛሬ ተጠናቋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የሦስት አገራት አምባሳደሮችን አሰናበቱ
Jun 30, 2025 195
አዲስ አበባ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በኢትዮጵያ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የካናዳ፣የስዊዲንና የሳኡዲ አረቢያ አምባሳደሮችን አሰናበቱ። ፕሬዝዳንቱ ያሰናበቱት የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ፣የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክና የሳኢዲ አረቢያ አምባሳደር ፋሃድ አልሁማያዳኒ (ዶ/ር) ናቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ ሦስቱም አምባሳደሮቹ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከአገራቱ ጋር በተለያዩ መስኮች የሁለትዮሽ ግንኙነትና ትብብር እንዲጠናከር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።   በተለይም የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲሳለጥ እንዲሁም በሌሎች የልማት የትብብር ዘርፎች ግንኙነቱ እንዲጠናከር ላደረጉት አስተዋጽዖም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አምባሳደሮቹ በሌሎች መስኮች ለአብነትም በመልሶ ማልማት ሥራዎች ጉልህ አስተዋጽኦ መደረጉን አንስተው፥ትብብሮች በቀጣይም ሊጠናከር እንደሚገባ ጠይቀዋል። በቀጣይ በተለይም ውጤታማ የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቶች ይበልጥ ሊጠናከሩ እንደሚገባ ጥሪ ማቅረባቸውን ውይይቱን የተከታተሉት የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አምባሳደር ትዝታ ሙሉጌታ ለኢዜአ ገልጸዋል። አምባሳደሮቹ በበኩላቸው፥ በኢትዮጵያ ቆይታቸው አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር በርካታ ሥራዎች መሥራታቸውንና በዚህም አመርቂ ውጤት መገኙቱን ጠቅሰዋል። የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ በቆይታቸው የካናዳና ኢትዮጵያን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማስፋት የሚያስችሉ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል።   በተመሳሳይ የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ በቆይታቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ቅድሚያ በሰጠባቸው መስኮች ትብብር በማድረግ አበረታች ሥራዎች ማከናወናቸውን አስረድተዋል። አምባሳደሮቹ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች እየተዘመገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውንና መሰል ሥራዎችን ሊያጠናክር እንደሚገባ ተናግረዋል። በቀጣይም ግንኙነቱ ይበልጥ እንዲጠናከር የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
በቀበሌ ደረጃ መንግስታዊ አገልግሎት ተደራሽ መደረጉ ቀልጣፋ አገልግሎት ከማስገኘቱ ባለፈ የልማት ተሳታፊነታችንን እያሳደገ ነው -ነዋሪዎች
Jun 30, 2025 104
ጭሮ ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በቀበሌ ደረጃ መንግስታዊ አገልግሎት ተደራሽ በመደረጉ ለአስተዳደራዊ ጉዳዮቻቸው ፈጣን ምላሽ ከማስገኘቱ ባለፈ የልማት ተሳታፊነታቸው እያደገ መምጣቱን የዞኑ ዶባ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። በዞኑ በአዲስ መልክ ለተዘረጋው የቀበሌ አስተዳደር አገልግሎት መስጫ የሚውሉ ጽህፈት ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ ነው። ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት ለህብረተሰቡ ቅርብ የሆኑ የቀበሌ መዋቅሮች ከዚህ ቀደም ትኩረት በማጣታቸው አገልግሎት ፍለጋ እስከ ወረዳ ማዕከላት ሲመላለሱ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት የቀበሌ ፅህፈት ቤቶች በዘመናዊ መልኩ ተገንብተው ሙሉ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን የተናገሩት በወረዳው የባቱ ቀበሌ ነዋሪ ኢብራሂም ሁሴን ናቸው።   በጤና፣ በትምህርት፣ በግብርና እና መሰል ጉዳዮች አገልግሎት ፍለጋ እስከ ወረዳ ማዕከል ድረስ ሲመላለሱ እንደነበር ያነሱት አስተያየት ሰጪው አሁን ላይ እነዚህን አገልግሎቶች በአካባቢያቸው በሚገኝ ቀበሌ ጽህፈት ቤት በቅርበት አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል። ከዚህ ቀደም በወረዳ ደረጃ ብቻ የሚያገኙትን የመሬት ነክ እና ግብርና አገልግሎቶችን በቀበሌ ማግኘታቸው የልማት ተሳታፊነታቸውን እያሳደገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አህመድ ኢብሮ ናቸው። ይህም የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን በማቃለል በአካባቢያቸው በሚከናወኑ የልማት ስራዎች ውስጥ ተሳትፏቸው እንዲጨምር ማድረጉንም ተናግረዋል። በብልጽግና ፓርቲ የዶባ ወረዳ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሙዘይን ከማል እንዳሉት በወረዳው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ በተጀመረው የቀበሌ አገልግሎት ማጠናከር ስራ ህብረተሰቡ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረግ ተችሏል። ሙሉ አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ በቅርበት እንዲሰጡ በመደረጉም አርሶ አደሩ ከግብርና ስራው እንዳይስተጓጎል ሁሉንም መንግስታዊ አገልግሎት በቅርበት እንዲያገኝ ማድረጉን ተናግረዋል። በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በሚገኙ 15 ወረዳዎችና አምስት ከተሞች የቀበሌ አደረጃጀቶችን በማጠናከር 3 ሺህ 522 ባለሙያዎች ተመድበው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ኢክራም ጠሀ ናቸው።   በዚህም 512 የቀበሌ ፅህፈት ቤቶች በዘመናዊ መልኩ እንዲገነቡ መደረጉን አመልክተዋል።  
መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደ ትናንቱ በትጋት ይሠራል - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Jun 29, 2025 218
  አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደ ትናንቱ በትጋት እንደሚሰራ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የአማራ ክልል ሕዝብ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መክፈል የማይገባውን ውድ ዋጋ በጥቂት ጥቅመኞች ምክንያት እየከፈለ መሆኑን ገልጿል። የፋኖን ታሪካዊ አነሣሥና ዓላማ ባልተከተለ አግባብ ራሳቸውን በፋኖ ስም የሚጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች በቀሰቀሱት ግጭትም የአማራ ክልል ሰላም እና ልማት ክፉኛ መጎዳቱን ጠቁሟል። መንግሥት ባለፉት ዓመታት ግጭቶችን ለማስወገድ በርካታ አማራጮችን ሲከተል መቆየቱ የሚታወስ ነው ያለው አገልግሎቱ ጥያቄ ያላቸዉ አካላትን በማቅረብ ለማነጋገር እና ለመደራደር በርካታ ጥረቶችን ማድረጉን ገልጿል ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- የአማራ ክልል ሕዝብ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መክፈል የማይገባዉን ውድ ዋጋ በጥቂት ጥቅመኞች ምክንያት እየከፈለ ይገኛል፡፡ የፋኖን ታሪካዊ አነሣሥ እና ዓላማ ባልተከተለ አግባብ ራሳቸዉን በፋኖ ስም የሚጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች በቀሰቀሱት ግጭት የአማራ ክልል ሰላም እና ልማት ክፉኛ ተጎድቷል፡፡ ፋኖ ሀገር በባዕድ ወራሪ እጅ በወደቀችበት እና ማእከላዊ መንግሥት በግዞት በቆየበት ወቅት ሀገርን ለማዳን የተደረገ ተጋድሎ የተመራበት ድንቅ ስያሜ ነው፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ግን የሀገሩን እና የክልሉን መንግሥት ለማፍረስ እና የባዕዳንን ተልእኮ ለማሳካት የተደራጁ ቡድኖች መጠሪያ ተደርጎ ሀገርን እና ሕዝብን ውድ ዋጋ አስከፍሏል፡፡ በሚሊዮኖች የሚቈጠሩ ታዳጊዎችን ከትምህርት ገበታ ነጥሏል፡፡ ሕዝብን ከልማት እንቅስቃሴዎች አሰናክሏል። የአማራ ክልል ሕዝብም የግጭት ጠማቂዎቹን እና የተላላኪዎቹን አጀንዳ በሚገባ ተገንዝቦ መንግሥት ሰላም እንዲያሰፍን በተደጋጋሚ ጥያቄዎችን በተለያዩ አግባቦች ሲያቀርብ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ የአማራ ክልል ሕዝብ ክልሉን ከግጭት እና ሥርዐት አልበኝነት ለማውጣት በየአካባቢዉ ተሰባስቦ ምክክር እና ውይይት አካሂዷል። የክልሉ ሕዝብ ጥያቄዎች በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን በአጀንዳነት እንዲያዙ አድርጓል፤ ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራዉ ቡድን ትክክለኛ የነፃነት ታጋይ መስሎት የተቀላቀለ ወጣት ወደ ሰላማዊ ሕይወቱ እንዲመለስ በሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ለምኗል፡፡ ከዚህም መሳ ለመሳ የፌደራል የፀጥታ ተቋማት እና የክልሉ የፀጥታ መዋቅር የክልሉን ሰላም ለማረጋጥ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፤ መሥዋዕትነትም ከፍለዋል፤ እየከፈሉም ነው፡፡ በዚህም በክልሉ አብዛኞቹ አካባቢዎች ሰላም ማስፈን ተችሏል፡፡ በተፈጠረው አስቻይ ሁኔታም የክልሉ ሕዝብ ከልማት ጥረቶች ወደ ኋላ እንዳይቀር በርካታ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል። ይሁን እንጅ በፀጥታ ኃይላችን ጥረት እና በሀገር ሽማግሌዎች ተማፅኖ አንጻራዊ ሰላም ቢሰፍንም ሕዝቡ በሚሻዉ ልክ የክልሉ ሰላም ሙሉ ለሙሉ አልተረጋገጠም፤ የዜጎች እንቅስቃሴ ከእገታና ዘረፋ ስጋት በምልዓት አልተላቀቀም፡፡ የነገ ሀገር ተረካቢዎች በተሟላ መልኩ ወደ ትምህርት ገበታ አልተመለሱም፡፡ የልማት እንቅስቀሴዎች ሕዝብ እና መንግሥት በሚሹት ልክ እንዲፋጠኑ ምቹ ድባብ አልሰፈነም፡፡ በዚህ ምክንያት ሕዝቡ ብሶቱን ለመንግሥት ጎላ አድርጎ ለማሰማት በተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን አካሂዷል፡፡ በሰላማዊ ሰልፎቹ መንግሥት የክልሉን ሰላም በማረጋገጥ ልማትን እንዲያጠናክር ሕዝቡ ጠይቋል፡፡ መንግሥት የውስጥ ባንዳዎችን እና የውጭ ኃይሎችን አደብ እንዲያስገዛለት፣ ልጆቹ ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱለት፣ ማሳውን ወደ መጎልጎልና ማረስ እንዲሰማራ፣ በኑሮው በሰላም ወጥቶ መግባት እንዲችል ምቹ ድባብ እንዲፈጠርለት፣ ሰላሙን በጋራ ለመጠበቅ እንደተዘጋጀ እና መንግሥት ሕግ ለማስከበር የጀመረዉን ጥረት በፅናት እንደሚደግፍ በሰላማዊ ሰልፎቹ ገልጿል፡፡ መንግሥት ባለፉት ዓመታት ግጭቶችን ለማስወገድ በርካታ አማራጮችን ሲከተል መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ ጥያቄ ያላቸዉ አካላትን በማቅረብ ለማነጋገር እና ለመደራደር በርካታ ጥረቶችን አድርጓል፡፡ በተደጋጋሚ የይቅርታ እና ምሕረት ጥሪዎችን አቅርቧል፡፡ በዚህም በርካታ በስሕተት የጥፋት ኃይሎችን ተቀላቅለዉ የነበሩ አካላት እጃቸዉን በመስጠት ሕይወታቸዉን አትርፈዋል፤ ሕዝቡን ለመካስ የሚያስችል የተሐድሶ ሥልጠናም አግኝተዋል፡፡ ነገር ግን አሁንም ጥቂት ጥቅመኞች የሕዝቡን ሰላም እያወኩ የባዕዳንን ተልእኮ ለማሳካት እየተወራጩ ይገኛሉ፡፡ መንግሥት የሕዝቡን የሰላም፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደትናንቱ ዝግጁ ነው፤ መንግሥታዊ ኃላፊነቱም ነው፡፡ የአማራ ክልል ሕዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ ከክልሉ ሕዝብ፣ ከክልሉ አስተዳደር እና የፀጥታ ኃይል ጋር በመቀናጀት መንግሥት የላቀ ጥረት ያደርጋል፡፡ ሕዝቡ ከመንግሥት ጋር በመቀናጀት ሰላሙን ለመጠበቅ ያሳየዉን ቁርጠኝነትም ያደንቃል፡፡ የሰላም በሮችን ዛሬም ክፍት አድርጎ እየጠበቀ የሕዝቡን የሰላም እና የልማት ጥያቄ ለመመለስ ከመቼዉም ጊዜ በላቀ ደረጃ ዝግጁ መኾኑንም መንግሥት ያረጋግጣል፡፡ የሰላም አማራጮችን የማይቀበሉ አካላትን በክልሉ የፀጥታ መዋቅር እና በፌደራል መዋቅር አማካኝነት አደብ በማስገዛት የሕዝቡን ሰላም ለማረጋገጥ ይሠራል፡፡ ሕዝቡ በአደባባይ ያቀረባቸዉን ጥያቄዎች ከሕዝብ ጋር ለመመለስ ያላሰለሰ ጥረት ያደርጋል፡፡ ሕዝቡ በሠለጠነ አግባብ ሐሳቡን በመግለጹም መንግሥት ምስጋና ያቀርባል፡፡ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
መንግስት ህግ በማስከበር ሰላምና ልማትን ለማጽናት እያደረገ ላለው ጥረት ተሳትፏችንን እናጠናክራለን
Jun 29, 2025 151
ደብረ ብርሃን፣ደብረ ማርቆስ፣ገንዳ ውሃና ወልዲያ፤ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦መንግስት ህግ በማስከበር ሰላምና ልማትን ለማጽናት እያደረገ ላለው ጥረት ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎች ገለጹ። በክልሉ ደብረ ብርሃን፣ደብረ ማርቆስ፣ መተማ ዮሐንስ እና ወልዲያ ከተሞች ሰላምን የሚደግፉና ጽንፈኝነትን የሚያወግዙ ህዝባዊ ሰልፎች ዛሬ ተካሂደዋል። በደብረ ብርሃን ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ሰልፍ የተሳተፉት አቶ ከፍያለው ግርማ በሰጡት አስተያየት የሰላም እጦት ችግር በውይይትና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ታጥቀው በጫካ ያሉ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ወደሰላም እንዲመጡና የሰላም ፍላጎታቸውን ለማሰማት በሰልፉ መታደማቸውን ተናግረዋል።   ኑሮውን ሎተሪ አዙሮ በመሸጥ የሚመራው ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ በፍቃዱ በለጠ በበኩሉ፥ሰርቶ ለማደግና ለመለወጥ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ገልጾ፣ ሰላም እንደሚፈልግ በጋራ ድምጹን ለማሰማት በሰልፉ መሳተፉን ገልጿል። የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የሰላም እጦት ችግሩን ለመፍታት መንግስት ህግ ከማስከበር ጎን ለጎን ለታጠቁ አካላት በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ማቅረቡን አስታውሰዋል።   የጥፋት ሀይሎች በህዝብና በሀገር ላይ እየፈጸሙት ያለውን የጥፋት ተግባር በማቆም የህዝብን ጽኑ የሰላም ፍላጎት በማክበር የመንግስትን የሰላም አማራጭ ሊቀበሉ ይገባል ብለዋል። በተያያዘ ዜና በደብረ ማረቆስ ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ሰልፍ ላይ የተሳተፉት ወይዘሮ እታገኝ አዳነ፥ ባለፉት ሁለት ዓመታት ያሳለፍነው ችግር እንዲያበቃ እንፈልጋለን፤ የእኛ ፍላጎት ዘላቂ ሰላምና ልማት ነው ብለዋል። ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም እንዲመጡ እንፈልጋለን ያሉት ወይዘሮ እታገኝ፣ ለአካባቢው ሰላም መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።   ሌላዋ ተሳታፊ ወይዘሮ አንለይ ተረፈ በበኩላቸው፥ ሰው በሰላም ወጥቶ መግባትና ሰርቶ መብላት የሚችለው ሰላም ሲኖር ነው ብለዋል።   ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ በላይ እንየው በበኩላቸው፥ በግጭት ሰቆቃ፣ መከራና ስቃይ እንጂ የሚመጣ ለውጥ የለም ፤ ሰላምን እንደምንፈልግ በይፋ ለመግለጽ ዛሬ በሰልፉ ላይ ተገኝተናል ብሏል። አንድነታችንን በማጠናከር ሰላምና ልማትን ማጽናት የትኩረት አቅጣጫችን ነው ያሉት ደግሞ የደብረ ማርቆስ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ ናቸው። "ህዝቡ ለሰላሙ ያሳየውን ቁርጠኝነት በማስቀጠል በከተማው የተጀመረው የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ፣የኮሪደር ልማትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እናበቃለን ብለዋል። የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ በበኩላቸው፥ ህብረተሰቡ በተባበረ ድምጽ ጽንፈኞች ከጥፋት ተግባራቸው እንዲታቀቡ ያሳየው ቁርጠኝነት ትልቅ አቅም ነው ብለዋል። በሌላ በኩል በመተማ ዮሐንስ ከተማ በተካሄደ ሰልፍ የተሳተፉት አቶ ጥላሁን ንጉሴ በበኩላቸው፥በአካባቢው ጸጥታ ችግር ምክንያት ህዝቡ በሰላም ወጥቶ መግባት ቀርቶ የተሻለ ህክምና እንኳ ለማግኘት ተቸግሮ እንደነበር አስታውሰዋል። መንግስት የጀመረውን የህግ የማስከበር ሥራ እንደሚደግፉ ገልጸው፣ በጫካ ያለው ሃይል የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበልና ሰላምን እንደምንፈልግ መልዕክት ለማስተላለፋ ሰልፍ መውጣታቸውን ተናግረዋል። ሌላኛዋ የሰልፉ ተሳታፊ ወይዘሮ ሲሳይነሽ ይርጋ በበኩላቸው፥ ፅንፈኝነት የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን ጭምር ሰለባ እያደረገ በመሆኑ ከመንግስት ጎን ሆነው ለመታገል ቁርጠኛ መሆናቸውን ነው የገለጹት። ጽንፈኝነትን ማውገዝ ብቻ ሳይሆን መታገልም ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የመተማ ዮሐንስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሀብቴ አዲሱ ናቸው። መንግስት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ልማትን ለማረጋገጥ የጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ህዝቡ ከመንግስት ጎን ሆኖ የሚያደርገውን አስተዋጾ እንዲያጠናክርም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ በወልዲያ ከተማ በተካሄደ ሰልፍ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሰላም እጦት ያተረፉት የሰዎች ሞት፣ እገታ፣ ዝርፊያና ስደትን ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። መንግስት ሰላም እንዲጠናከር ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች ወደሰላም እንዲመጡ ያቀረበውን ጥሪ እንደሚደግፉ ገልጸው፣ የጥፋት ሀይሎች ጥሪውን በመቀበል ወደሰላም እንዲመጡ ጠይቀዋል። የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፥የጽንፈኞች እኩይ ሴራ የልማት ሥራን እንዳያደናቅፍ ጠንክሮ መታገል ይገባል ብለዋል። የታጠቁ ሃይሎችም የህዝብን ድምጽ በመስማትና በማክበር መንግስት በተደጋጋሚ ያቀረበውን የሰላም አማረጭ ተቀብለው ህዝባቸውን እንዲክሱም ከንቲባው አስገንዝበዋል። በተለያዩ ከተሞች በተካሄዱ ህዝባዊ ሰልፎች ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለሰላም ጽኑ ፍላጎት እንዳላቸውና ጽንፈኝነት ሀገርና ህዝብን ስለሚጎዳ ለሰላማቸው ከመንግስት ጎን እንደሚቆሙ ገልጸዋል።
ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እና ልማት እንዲፋጠን ድጋፋችንን እናጠናክራለን
Jun 29, 2025 165
ባህርዳር፤ ሰኔ 22/2017 (ኢዜአ) በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እና የልማት ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በባህርዳር ከተማ የህዝባዊ ሰልፍ ተሳታፊዎች ገለጹ። በባህርዳር ከተማ ‘‘ሀገርን ለማፅናት እና ለማበልፀግ ከመንግስት ጎን እንሰለፋለን’’ በሚል መሪ ሀሳብ ሰላምን የሚደግፍ ህዝባዊ ሰልፍ ዛሬ ተካሂዷል። ከሰልፉ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ትዕዛዙ ገብረኢየሱስ ለኢዜአ እንደገለጸው በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ ለህዝቡ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው።   በክልሉ አሁን ላይ ባለው ሰላም በከተማው ልማት እንዲፋጠንና የወጣቶች ተጠቃሚነት እያደገ እንዲመጣ ማስቻሉን ገልጿል። የተገኘው ሰላም ዘላቂ እንዲሆንና የልማት ስራዎች እንዲጠናከሩ ተሳትፏችንን እናጠናክራለን " ያለው ወጣት ትዕዛዙ የታጠቁ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም እንዲመጡ ጠይቋል ። "የሰላም እጦት የሚያስከትለው ጥፋት በመሆኑ ለሰላም ዘብ ለመቆም ቆርጠን ተነስተናል" ያሉት ደግሞ የሰልፉ ታዳሚ ወይዘሮ አስረሱ ጌትነት ናቸው። በከተማው አሁን ላይ ባለው ሰላም ተስፋ ሰጭ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን ተናግረዋል።   "በጫካ ላሉ የታጠቁ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላም ሊመጡ ይገባል" ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል። ‘‘በክልላችን ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ ድምፃችንን ለማሰማት በሰልፉ ተሳትፈናል ’’ ያለው ደግሞ ወጣት ሳለአምላክ አድማሱ ነው። ሰላም ለአንድ ወገን የሚተው አለመሆኑን ጠቁሞ "ሁላችንም ከመንግስት ጎን በመሰለፍ ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ልማት እንዲረጋገጥ በቁርጠኝነት ልንሰራ ይገባል" ብሏል።   የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው የከተማው አስተዳደር ሰላምን በማጽናት ልማትን ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። "ፅንፈኛው ኃይል በክልሉና በከተማችን ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት አድርሷል" ያሉት አቶ ጎሹ ህፃናት ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ ማድረጉን ጠቅሰዋል። የፅንፈኛው ሀይል የክልሉን ልማትና ዕድገት ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ህብረተሰቡ በዛሬው ሰልፍ ጽንፈኝነትን በማውገዝ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የደገፈበት መሆኑን ተናግረዋል ።   ጫካ የሚገኙ ኃይሎች የሰላም ጥሪን ተቀብለው ህዝባቸውን እንዲክሱም አሳስበዋል። በከተማው ሰላምን ዘላቂ ለማድረግና ልማትን ለማፋጠን እየተደረገ ባለው ጥረት የህብረተሰቡ ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ይኽው የህዝቡ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል ። በሰልፉ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ማህበራዊ
አዋጁ በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች መብታቸውና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የሚያስችል ነው
Jul 1, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች መብታቸውና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የሚያስችል መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 41ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅን መርምሮ አጽድቋል፡፡ አዋጁን አስመልክቶ የተዘጋጀውን የውሳኔ ሀሳብ በምክር ቤቱ የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) አቅርበዋል፡፡ በዚህም አዋጁ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በተመለከተ ቀደም ሲል ሲሠራባቸው የነበሩት አዋጆች ክፍተቶች የነበሩባቸው በመሆኑና በጊዜ ሂደት አዋጆቹ ያላካተቷቸውን ጉዳዮችን በመለየት ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል አዋጅ እንደሆነ ተናግረዋል። የቀድሞዎቹ አዋጆች የቤት ውስጥ ሠራተኛ፣ የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ ውጭ የትምህርት ዝግጅት የማይጠይቁ የሥራ ዓይነቶችን ባለማካተታቸው ክፍተቶች የተፈጠሩ ስለመሆኑም አንስተዋል። አዋጁ ሕገ- ወጥ የውጪ ሀገር የሥራ ስምሪትን ለመከላከልና በውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት የዘመነ የአንድ ማዕከል የአሠራር ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚያስችልም ጠቅሰዋል፡፡ በውጭ ሀገራት ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች መብታቸውና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የሚያስችል ላኪ ኤጀንሲዎች ተመጣጣኝ የዋስትና ገንዘብ እንዲያስቀምጡ በማድረግ የዜጎችን እንግልት የሚያስቀር አዋጅ በመሆኑ ነው ብለዋል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ዜጎች ለህገ ወጦች ሳይጋለጡ በአግባቡ ሰልጥነው ተመዝነው እንዲሰማሩ የሚያደርግ ነው ብለዋል።   በአዋጁ ጠንካራ የሆነ የስልጠናና የምዝና ስርዓት እንደ አንድ ጠንካራ ስርዓት ተደርጎ መካተቱን ሚኒስትሯ ተናግረዋል።     የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ አዋጁ ዜጎችን ከህገ ወጥ ደላሎች የሚታደግና የዜጎችን ክብርና ደህንነት የሚያስጠብቅ ነው ሲሉ ተናግረዋል።  
በዩኒቨርሲቲው የተደረገልን አቀባበል በተረጋጋ መንፈስ ለመፈተን አስችሎናል-የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች
Jul 1, 2025 248
ዲላ፣ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ) ፦በዲላ ዩኒቨርሲቲ የተደረገላቸው አቀባበል እና ለፈተናው ያደረጉት ዝግጅት በተረጋጋ መንፈስ ለመፈተን እንዳስቻላቸው በዩኒቨርሲቲው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ገለጹ። ተማሪዎች ከሥነ ልቦና ጫና ነጻ ሆነው ፈተናውን በተረጋጋ መንፈስ እንዲወስዱ የተቀናጀ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል።   አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች መካከል በሻኪሶ ወረዳ የማጋዶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ኤፍራታ ዮሐንስ እንደገለጸችው፣ በዩኒቨርሲቲው የተደረገላቸው አቀባበል እና እያገኙት ያለው የተማሪዎች አገልግሎት ፈተናውን በእርጋታ ለመውሰድ አስችሏታል። በበይነ መረብ እየተሰጠ ያለው ፈተና ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀምና ኩረጃን ለማስቀረት ማስቻሉን የተናገረው ደግሞ ሌላው ተፈታኝ ተማሪ አማኑኤል ሽፍራው ነው።   በዩኒቨርሲቲው የተደረገላቸው አቀባበልና ለፈተናው ሲያደርጉት የነበረው ዝግጅት ፈተናውን በተረጋጋ ሁኔታ ለመውሰድ እንዳስቻላቸውም ተናግሯል። በዲላ ከተማ አስተዳደር የቆፌ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ትዝታ ግርማ በበኩሏ ፈተናውን ተረጋግተው እንዲሰሩ ባለድርሻ አካላት እገዛ ማድረጋቸውን ጠቅሳለች።   በእዚህም ሀሳባቸውን ፈተናው ላይ ብቻ በማድረግ በተዘጋጁት ልክ ፈተናውን እየወሰዱ መሆኑን ጠቅሳ፣ በፈተናው ስኬታማ ለመሆን የራሷን ዝግጅት ስታደርግ መቆየቷን አስታውሳለች። በትምህርት ሚኒስቴር የዲላ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል ሃላፊ አቶ እስክንድር ላቀው በበኩላቸው እንዳሉት በዩኒቨርሲቲው ከ7 ሺህ ለሚበልጡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናው በበይነ መረብና በወረቀት እየተሰጠ ነው።   ተማሪዎች ከሥነ ልቦና ጫና እና ተጽእኖ ነጻ ሆነው ፈተናውን በተረጋጋ መንፈስ እንዲወስዱ የተቀናጀ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም አስረድተዋል። ለተፈታኝ ተማሪዎች ከአቀባበል ጀምሮ የምክርና የተለያዩ አገልግሎቶች በቅርበት እየተሰጠ መሆኑን አንስተው ይህም ተማሪዎች ትኩረታቸው ፈተናው ላይ ብቻ እንዲሆን ማድረጉን ጠቁመዋል። ፈተናው በዩኒቨርሲቲው ሦስት ግቢዎች እየተሰጠ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ ዓለሙ (ዶ/ር) ናቸው።   ኩረጃን ለማስቀረት ተማሪዎች የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ወደፈተና ቦታ ይዘው እንዳይገቡ መደረጉን ጠቁመው በዩኒቨርሲቲው በኩል ለተፈታኝ ተማሪዎች የማደሪያ፣ የምግብና ሌሎች አገልግሎቶችን በማቅረብ ተረጋግተው እንዲፈተኑ መደረጉን ገልጸዋል።  
በክልሉ ግንባታቸው የተጓተቱ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ ነው
Jul 1, 2025 81
ቦንጋ፤ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግንባታቸው የተጓተቱ የልማት ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። ምክትል ርዕሰ መሰተዳድሩ ከ53 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባውን የአውራዳ ኢንዱስትሪያልና ኮንስትራክሽን ኮሌጅን ዛሬ መርቀዋል።   ኢንጂነር ነጋሽ (ዶ/ር) እንደገለጹት በክልሉ ግንባታቸው የተጀመሩ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ አንጻር ጉልህ ሚና ቢኖራቸውም በተለያዩ ምክንያቶች ተጓትተው ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅትም የተጓተቱ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለይቶ ግንባታቸውን በማፋጠን ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ክልሉ ራሱን ችሎ ከመቋቋሙ በፊት ተጀምረው የነበሩ 10 የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችን ለማጠናቀቅ በተሰራው ሥራ በዚህ ዓመት ሦስቱን ማጠናቀቅ እንደተቻለ ጠቅሰው፣ ቀሪዎችን በቀጣይ ዓመት የማጠናቀቅ ሥራ ይሰራል ብለዋል።   በክልሉ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በክህሎት የበቁ ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን ከማፍራት ባለፈ ተኪ ምርት ለማምረት የሚያደርጉትን ጥረት ለማጠናከር እንደሚሰራም ኢንጂነር ነጋሽ (ዶ/ር) አመልክተዋል። ለኮሌጁ ግንባታ ከ53 ሚሊዮን 800 ሺህ ብር በላይ ወጪ መደረጉን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አብይ አንደሞ (ዶ/ር) ናቸው። ኮሌጁ በውስጡ ለመማሪያ ክፍል፣ ለቤተመጻህፍት፣ ለመሰብሰቢያ አዳራሽና ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ ባለሁለት ወለል ህንጻዎችን አካቶ የተገነባ መሆኑንም ተናግረዋል።   ዜጎች ከሥራ ጠባቂነት ተላቀው ሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ የሚያስችላቸውን ሙያና ክህሎት የሚጨብጡበት መሆኑንም አመልክተዋል። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንደሻው ከበደ በበኩላቸው፣ ዛሬ ለምረቃ የበቃው ፕሮጀክት በክልሉ የዘገዩ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አንድ ማሳያ ነው" ብለዋል።   በኮሌጁ ያልተሟሉ ግብዓቶችን ለማሟላት በተቀናጀ መንገድ እንደሚሰራ ተናግረው፣ ኮሌጁ ብቃት ያላቸውን ዜጎች አሰልጥኖ ለማውጣት በሚያደርገው ጥረት ዞኑ የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የኮሌጁ መመረቅ የአካባቢውን ህብረተሰብ የቆየ የልማት ጥያቄ መልሷል ያሉት ደግሞ የአውራዳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ታረቀኝ ሀይሌ ናቸው። ኮሌጁ የበለጠ እየተጠናከረ እንዲመጣ በወረዳው በኩል ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።   በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው እንዲሁም የክልሉ ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ በላይ ተሰማን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገንተዋል። አመራሮቹ በኮሌጁ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል።  
ኢኮኖሚ
በክልሉ ከህዝብ ቁጥር ጋር የሚጣጣም የኢኮኖሚ እድገት እንዲኖር ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው
Jul 1, 2025 61
ሀዋሳ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ከህዝብ ቁጥር ጋር የሚጣጣም የኢኮኖሚ እድገት እንዲኖር ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ገለፀ። ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የክልሉን የሥነ-ህዝብ ምክር ቤት ጉባኤ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ዛሬ አካሂዷል፡፡ የቢሮው ኃላፊ አራርሶ ገረመው(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ በክልሉ የህዝብ ቁጥር እየጨመረ ከመምጣት ባለፈ ከፍተኛ የህዝብ ጥግግት አለ፡፡ በየጊዜው እያደገ ከሚመጣው የህዝብ ቁጥር ጋር የሚጣጣም የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገቡ ለመቀጠል ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ለዚህም ቢሮው ከግብርና፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከአገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች ጋር ተባብሮ በመስራት እየተመዘገበ ያለውን የኢኮኖሚ ዕድገት ከህዝብ ቁጥር ዕድገት ጋር ለማጣጣም እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የህዝብ ቁጥርን ወደ መልካም ዕድል በመቀየር በእውቀት የበቁ ዜጎችን ለማፍራት፣ ህዝቡ ከቴክኖሎጂ ጋር ያለውን ቁርኝት ለማሳደግ፣ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመርና ለመሰል ሥራዎች ቢሮው ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅት የሴክተር ተቋማትን የአምስት ዓመታት አጠቃላይ ዕድገት ጠቋሚዎች ዝርዝር የያዘ የመረጃ ቋት መዘጋጀቱን ጠቅሰው፣ ይህም ባለድርሻዎች በተደራጀ መረጃ ላይ የተመሰረተ ሥራ ለመስራት ያስችላቸዋል ብለዋል፡፡ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዘማች ሂርጢባ የግብርናው ሴክተር ከክልሉ ጥቅል ምርት እድገት ከ43 በመቶ በላይ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ የሚመዘገበውን ዕድገት ለማስቀጠልና የህዝብን ቁጥር ታሳቢ ያደረገ የግብርና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ከፕላንና ልማት ቢሮ ጋር ተናበን እየሰራን ነው ሲሉም ገልጸዋል። በክልሉ ያለውን የእርሻ መሬት መጠን የመለየት ሥራ መከናወኑን ጠቁመው ለእርሻ ሥራ በቂ መሬት የሌላቸውን በእንስሳት ልማትና በሌሎች ሥራዎች እንዲሰማሩ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።፡ የሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ ግብዓት ጥራት ቁጥጥር አግልግሎት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ቡሪሶ ቡላሾ በዕቅድ የሚመራ ቤተሰብ እንዲኖርና የመኖር ምጣኔው ከፍ ያለ ማህበረሰብ ለመገንባት በትብብር ይሰራል ብለዋል፡፡ በዚህ ረገድ የተያዙ ግቦችን ለማሳካት የጤና መሠረተ ልማቶችን የማስፋፋት እንዲሁም ግብዓቶችን በበቂ ሁኔታ የማሟላት ሥራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ነው ያሉት፡፡ በዚህም በክልሉ የመኖር ምጣኔን ከተቀመጠው የመኖር ምጣኔ ጋር ማጣጣም መቻሉን ጠቅሰው፣ የወሊድ ምጣኔንም ወደ 3 ነጥብ 91 ማውረድ ተችሏል ብልዋል።፡ በጉባኤው የሚመለከታቸው ሴክተር ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የባህል ሽማግሌዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በሸገር ከተማ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - አስተዳደሩ
Jul 1, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ። በከተማው በኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዛሬ ተጀምሯል። በከተማው በበጀት ዓመቱ ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ የተገነቡ የመሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።   የከተማው ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) በምረቃ ሥነስርዓቱ እንደገለጹት የከተማዋን ልማት በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው። በበጀት ዓመቱ በ17 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር 384 ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው፣ ከእነዚህ ውስጥ የ308ቱ ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ በቅተዋል ብለዋል። ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል የመስኖና የመጠጥ ተቋማት፣ ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣቢያ፣ መንገዶች፣ ፖሊስ ጣቢያ እና የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች ግንባታን በማሳያነት ጠቅሰዋል።   የኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ ሀላፊ ጫላ ደሬ በበኩላቸው ለህብረተሰቡ የልማት ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ለመስጠት ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ በክፍለ ከተማው ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ 24 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ሥራ መጠናቀቁን ተናግረዋል። የህዝብን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፣ ህዝቡም ለፕሮጀክቶች ስኬታማነት እያደረገ ያለውን ተሳትፎ እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል። ከልማት ፕሮጀክቶቹ ምረቃ በተጨማሪ የከተማው ነዋሪዎችን ያሰተፈ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በከተማው ኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ ድሬ ሶኮሩ ወረዳ ዛሬ ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) እንዳሉት በክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ከ40 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ለምግብነት፣ ለደንና ለውበት የሚውሉ ችግኞች ይተከላሉ።   በተመረጡ ክፍለ ከተሞችም የአቮካዶና የአፕል ችግኞችን በመትከል በክልስተር የማልማት ስራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል። በችግኝ ተከላው ከተሳተፉ የኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ በቀለ ያኢ እና አቶ በላቸው አበራ ችግኝ ከመትከል ባለፈ በየጊዜው በመንከባከብ ለማሳደግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ መትከል የአየር ንብርት ለውጥን ለመቋቋምና ምርታማነትን ለማሳደግ ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ በየዓመቱ በአረንጓዴ አሻራ ልማት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ችግኝ በመትከል አሻራቸውን ማኖራቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸው፣ በቀጣይም የተከሏቸውን ችግኞች በመንከባከብ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል።
የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው
Jul 1, 2025 59
  አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ። አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ በስፔን ሲቪያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በኮንፍረንሱ እየተሳተፈ ነው። ሚኒስትሩ በኮንፍረንሱ ባደረጉት ንግግር ከ10 አመት በፊት በአዲስ አበባ ሶስተኛው ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይሁንና በኮንፍረንሱ የጸደቀው የአዲስ አበባ የድርጊት መርሃ-ግብር የአተገባበር ተግዳሮት እንደገጠመው ጠቅሰው የሲቪያ ስምምነት ይህንን ተግዳሮት የሚሻገር መሆን እንደሚገባው አመልክተዋል። ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመተግበር ከሚያስፈልገው ፋይናንስ ውስጥ የ4 ትሪሊዮን ዶላር እጥረት መግጠሙን አንስተዋል። ይህ ሁኔታ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራትን ለዘርፈ-ብዙ ተግዳሮቶች ዳርጓቸዋል ነው ያሉት ሚኒስትሩ። ለአብነትም አዳጊ ሀገራት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ ለሚመጡ ቀውሶች እና ለእዳ ጫና መጋለጣቸው አሳሳቢ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ኮርፖሬሽኖች ላይ ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ የታክስ ስርዓትን መተግበርና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጥላ ስር በየነ-መንግስታዊ የብድር አስተዳደርን በማቋቋም ዘላቂ ያልሆነ የብድር ችግሮችን መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል። በተጨማሪም የልማት ፋይናንስ ድጋፎችና ብድሮች ሀገራት ቅድሚያ ከሚሰጣቿው ጉዳዮችና እቅዶች ጋር መጣጣም እንዳለባቸውና አዳጊ ሀገራት የሚያገኙት የፋይናንስ ድጋፍ መጨመር እንዳለበት አመልክተዋል። በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ዘላቂ እና ተገማች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖራቸውና ቀውሶችን በተገቢው መንገድ ማስተዳደር እንዲችሉና ዓለም ዓቀፍ የልማት ፋይናንስ ስምምነቶች በተገቢው እንዲተገበሩ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ሊኖር እንደሚገባም ነው የገለጹት። በአፍሪካ እና በአጠቃላይ አዳጊ ሀገራት በመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ የስራ ዕድል ፈጠራና የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የሚያስችል የፋይናንስ አቅርቦት በአስተማማኝ መልኩ ማቅረብ ድህነትን ለመቀነስ እና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ሚኒስትሩ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን “ዓለም አቀፍ ትብብርን በአዲስ መልክ ማደስ” በሚል ርዕስ በሚኒስትሮች ደረጃ በተደረገው ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል። ሁለተኛው ቀኑን የያዘው አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ልዑክ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን እየተካሄዱ ባሉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል።
በዞኑ የተገነቡ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የሕብረተሰቡን ችግሮች እየፈቱ ነው
Jul 1, 2025 54
መቱ ፤ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፡- በኢሉ አባቦር ዞን የተገነቡ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የሕብረተሰቡን ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እየፈቱ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳደሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ አስታወቁ። የኦሮሚያ ክልል የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በኢሉአባቦር ዞን አሌ ወረዳ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የኢሉአባቦር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ በዞኑ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ በውጤታማነት ተጠናክረው ቀጥለዋል። ባለፉት ዓመታት በዞኑ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ተቋማት የሕብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በመፍታት ተጠቃሚነቱን በተግባር እያረጋገጡ መሆኑን ገልጸዋል። እየተገባደደ በሚገኘው በጀት ዓመትም በግንባታ ላይ የቆዩ 656 ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውንም አረጋግጠዋል። የአሌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ዮሐንስ ከበደ፣ በወረዳው በ153 ሚሊዮን ብር በጀት የተገነቡ 23 የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን አስታውቀዋል።   ለአገልግሎት ከበቁት ፕሮጀክቶች መካከል የመጠጥ ውሃ ተቋማት፣ ድልድዮችና የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ይገኙበታል ብለዋል።   በምርቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መሐመድሳኒ አሚን በበኩላቸው፤ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ሌሎች የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር ማነቃቂያ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተለይ እንደ ድልድይና መንገድ ያሉ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የሕብረተሰቡን ትስስር ከማጠናከር ባሻገር ለኢኮኖሚያዊ ልማት ንቅናቄ ትልቅ አቅም የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል።   ሕብረተሰቡም የተገነቡና በሂደት ላይ የሚገኙ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶቹን በመጠበቅና በመንከባከብ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ የድርሻውን እንዲወጣ መልዕክት አስተላልፈዋል። በአሌ ወረዳ የኦንጋ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ለዘመናት የነበረባቸውን የንጹሕ መጠጥ ውሃ እጥረት ያቃለለላቸው መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቀበሌው ነዋሪ አቶ ሁሴን ከበደ ናቸው።     አቶ ግርማ አባተ እና አቶ ያደታ ዲሳሳ ደግሞ በወረዳው የኦኖኑ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ፤ በአካባቢው የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረው ድልድይ ምላሽ በማግኘቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ስልጠና አካዳሚ ለአፍሪካ ሀገራት ተመራጭ የስልጠና ማዕከል እየሆነ ይገኛል - የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን በለስልጣን
Jul 1, 2025 79
አዲስ አበባ፤ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የስልጠና አካዳሚ ለበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ቀዳሚ ተመራጭ የስልጠና ማዕከል እየሆነ እንደሚገኝ የኤር ናቪጌሽን ሬጉሌሽን አገልግሎት ዳይሬክተር እና የአካዳሚው ተጠባባቂ ዳይሬክተር ልዑልሰገድ ጉልላት ገለጹ። ዳይሬክተሩ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ አካዳሚው ለአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ውጤታማነት ባለሙያዎችን በማፍራት ላይ ይገኛል ብለዋል። ለበርካታ ዓመታት በአየር ትራፊክ ቁጥጥር፣ በኮሙኒኬሽን እና ናቪጌሽን ሰርቪላንስ (CNC) ዘርፍ በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ብቁ የአቪዬሽን ባለሙያዎችን በማሰማራት ላይ መሆኑንም ጠቅሰዋል።   በዚህ ዓመት ብቻ ከ86 በላይ ባለሙያዎችን በንድፈ ሃሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ወደ ሥራ ማስገባቱን አንስተዋል። አካዳሚው የሚሰጠው ስልጠና ከሀገር አልፎ ለጎረቤት ሀገራትና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ውጤታማ ስልጠና እየሰጠ ተፈላጊነቱን እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። በቅርቡ ከጅቡቲ፣ ከሶማሊያ እንዲሁም ከኮሞሮሶና ሌሎች ሀገራት የመጡ የአቪዬሽን ሰልጣኞችን ማሰልጠኑን ተናግረዋል። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን የስልጠና አካዳሚ ሙያተኞቻቸውን ለማሰልጠን ጥያቄ እያቀረቡ እና ተመራጭ እያደረጉት መሆኑን ተናግረዋል። አካዳሚው በአፍሪካ ትልቅ ስምና ተቀባይነት እንዳለው በማንሳት፥ ይበልጥ ቀጣናውን ለማስተሳሰር በርካታ ተግባራትን በትኩረት እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።   በአካዳሚው አሰልጣኝ እና ዋና የአየር ተቆጣጣሪ ቤተልሔም ሞላ በበኩላቸው፥ ስልጠናው የዓለም አቪዬሽን ኢንዱስትሪ በደረሰበት ደረጃ ልክ እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተግባር እና በንድፈ ሀሳብ የተደገፈው ስልጠና ሰልጣኞች ተግባራዊ የሆነ በቂ እውቀት የሚያገኙበት እና በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ውጤታማ የሚያደርጋቸው ነው ብለዋል። ባለፉት ሰባት ወራት በብቁ አሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና መውሰዱን የገለጸልን ደግሞ ከድሬዳዋ የመጣው ምንተስኖት አለማየሁ ነው።   በአቪዬሽን ዘርፉ በተሰማራበት ሙያ ለማገልገል ካለው ተነሳሽነት በተጨማሪ፥ በስልጠናው ያገኘው እውቀት ትልቅ አቅም እንደፈጠረለትም ተናግሯል።        
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በዲጂታል ስርዓቱ ከፍተኛ ውጤት አስገኝቷል-ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)
Jul 1, 2025 90
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፦ባለፉት አምስት አመታት ሲተገበር የቆየው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በዲጂታል ስርዓቱ ውጤት አስገኝቷል ሲሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት የአንድን ሀገር ሁለንተናዊ እድገት ማረጋገጥ የሚቻለው የአሰራር ስርዓትን በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በኢኖቬሽን ሲደገፍ ነው። ኢትዮጵያም ወደ ዲጂታል ስርዓት መግባት የሚያስችላትን የህግ ማዕቀፍ እንዲሁም ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ስራ እንደገባች ገልጸዋል። በተጨማሪም ወደ ዲጂታል ስርዓቱ መግባት የሚያስችሉ መሰረተ ልማቶች ተሟልተው ተግባራዊ መደረግ መጀመራቸውን አስታውቀዋል። ስትራቴጂው ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያና የ10 አመት መሪ የልማት ዕቅድ ስትራቴጂዎች እንዲሁም ከአፍሪካ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ ጋር ተሳስሮ ሲተገበር መቆየቱንም ገልጸዋል። ባለፉት አመታት ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጠናቀቅ ገልፀው በቀጣይ 2030 ድረስ ተግባራዊ የሚደረገው የ5 አመት ስትራቴጂ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ ነው የጠቀሱት። ባለፉት አምስት አመታት ሲተገበር የቆየው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በሳይንስ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዘርፉ ላይ አመርቂ ውጤቶች እንደተመዘገቡቡት ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። ባለፉት አምስት አመታት የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በመዘርጋት፣ የዲጂታል አገልግሎት በማስፋት እንዲሁም የዲጂታል መታወቂያ ተደራሽ ከማድረግ አኳያ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸው አንስተዋል። የመንግስትን የአሰራር ስርዓት ከማዘመን ጋር በተያያዘ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025ን እውን ለማድረግ ከተሰሩ ስኬታማ ስራዎች መካከል መሆኑን ገልፀዋል። ማዕከሉ በአንድ ጣራ ስር የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተለያዩ የመንግስት አገልግሎቶችን በማጣመር አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ በቀጣይም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ወደ ክልል ከተሞች በማስፋት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።        
በክልሉ በዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ በተቋማት የአገልግሎት አሰጣጡን የማሻሻል ስራ በስፋት እየተከናወነ ነው
Jul 1, 2025 62
ሀዋሳ ፤ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ) ፡-በዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ በእውቀትና ክህሎት የዳበሩ ባለሙያዎችን በማፍራት በተቋማት የአገልግሎት አሰጣጡን የማሻሻል ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በክልሉ ለዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡   የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስን የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አሰፋ ጉራቻ፤ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የተገልጋዮችን ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችሉ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን አንስተው ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በተደረገ የዳሰሳ ጥናት የተገልጋዮች እርካታ ከ47 በመቶ ወደ 66 ነጥብ 3 በመቶ ከፍ ማለቱ ተመላክቷል። ለመሻሻሉ ምክንያት የማዘጋጃ ቤቶች፣ ትራንስፖርት፣ የገቢዎችን ጨምሮ 7 የተለያዩ ሴክተሮችን የአገልግሎት ክፍተቶች በመለየት በቴክኖሎጂ ጭምር የታገዘ አሰራር በመዘርጋት መሆኑን አስረድተዋል። በቀጣይም አገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ለማጠናከር በድጅታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር በመዘርጋት በእውቀትና በክህሎት የዳበረ አገልጋይ የመፍጠር ትኩረት ይደረጋል ሲሉ አረጋግጠዋል። ለተመደቡበት የሥራ ዘርፍ ቃላቸውን ጠብቀውና ሃላፊነት ወስደው የማገልገል ችግር ያለባቸው አመራርና ሰራተኞች ሲያጋጥሙ በአሰራሩ መሰረት እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም ተናግረዋል።   የሲዳማ ክልል ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ዳይሬክተር ወይዘሮ ታደለች ዮሐንስ፤ በቢሮው እየተደረጉ ያሉ የአሰራር ማሻሻያዎች እንዲሁም የድጋፍና ክትትል ስራዎች ለውጥ ማምጣታቸውን አንስተዋል። በዚህም የአገልጋዮች አቅም እየዳበረ የተገልጋዮች እርካታም እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግረዋል።፡ በሥልጠናው ከ240 በላይ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡    
ኢትዮጵያ የጨረር ህክምና ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jun 30, 2025 118
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የካንሰር ምርመራን ጨምሮ የጨረር ህክምና ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የጤና ሚኒስቴር ከዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር "የተስፋ ጨረሮች በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጁትና አቶሚክ ኢነርጂ በጤናው ዘርፍ ባለው ጠቀሜታ ዙሪያ የሚመክር ዓለም አቀፍ ጉባኤ በአፍሪካ ህብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል። በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ጀነራል ራፋኤል ግሮሲ፣ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ታድመዋል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፥ የዓለም የጤና አውድ እየተቀየረ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያም ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን ታሳቢ ያደረገ የጤና ስርዓት እየገነባች ነው ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በጤና ኤክስቴንሽን አማካይነት በተሰራው ስራ የበርካቶችን ጤና አጠባበቅ ማሻሻል መቻሉን ገልጸዋል። በርካታ የጤና ባለሙያዎችም ሰልጥነው አገልግሎት እየሰጡ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በሁሉም አካባቢ የጤና አገልግሎትን በጥራት ተደራሽ የማድረግ ጉዞ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። ኢትዮጵያ የካንሰር ምርምራና የጨረር ህክምና ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝ በማንሳት፥ ለዚህም ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም መጀመሯን ጠቁመዋል። የጨረር ህክምና በጥንቃቄ እና በኃላፊነት ጥቅም ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋቱን አመላክተዋል። የኑክሌር ኢነርጂን ለጤና አገልግሎት በማዋል የጨረር ህክምናን ማስፋት የካንሰር በሽታን በፍጥነት በምርመራ በመለየት የሰዎችን ህይወት ለመታደግ ትልቅ ሚና እንዳለውም ነው የገለጹት።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘውም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የህብረተሰብን ጤና በማሻሻል ንቁና ጤናማ አኗኗርን እያጎለበተ መሆኑን አንስተዋል። የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የኑክለር ኢነርጂን ለሰላማዊ አገልግሎት በተለይም ለጤናው ዘርፍ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያደርጋቸው ድጋፎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የልማት አጋሮች እና መንግስታት ከፈንድ ባሻገር የዓለም ጤና ውጤት ፈጣሪዎች በመሆን የትብብር አድማሳቸውን ከፍ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።
ስፖርት
የአውሮፓ ስመ ገናናዎቹ  ሪያል ማድሪድ እና ጁቬንቱስ ጨዋታ ተጠባቂ ነው 
Jul 1, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሃ ግብር የመጨረሻ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሀርድ ሮክ ስታዲየም ሪያል ማድሪድ ከጁቬንቱስ የሚያደርጉት ጨዋታ የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪያን ቀልባቸውን ጥለውበታል። የአምስት ጊዜ የፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ አሸናፊው ሪያል ማድሪድ በምድብ ስምንት በሰባት ነጥብ የምድቡ መሪ በመሆን ማጠናቀቁ ይታወቃል። በውድድሩ የመጀመሪያ ተሳትፎውን እያደረገ የሚገኘው ጁቬንቱስ በምድብ ሰባት ስድስት ነጥብ በማግኘት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ወደ ጥሎ ማለፉ ገብቷል። የአውሮፓ ኃያላኑ ሪያል ማድሪድ እና ጁቬንቱስ በሁሉም ውድድሮች እስከ አሁን 21 ጊዜ ተገናኝተዋል።   ሪያል ማድሪድ 10 ጊዜ በማግኘት ውስን ብልጫ ወስዷል። ጁቬንቱስ 9 ጊዜ ሲያሸንፍ 2 ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። በ21ዱ ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ 26 ግቦችን ሲያስቆጥር ጁቬንቱስ 25 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሁለቱ ክለቦች ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት እ.አ.አ በ2017 በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ነበር። በካርዲፍ በተካሄደው ጨዋታው ሪያል ማድሪድ 4 ለ 1 በማሸነፍ ዋንጫውን አንስቷል። በአውሮፓ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ትልቁ የክለቦች ባላንጣነት ማሳያ ተደርጎ የሚጠቀሰው የቡድኖቹ ፍልሚያ ሁሌም ጠንካራ እና እልህ አስጨራሽ ፉክክር የሚደረግበት ነው። ሪያል ማድሪድ እና ጁቬንቱስ የየሊጋቸውን ዋንጫ በተመሳሳይ 36 ጊዜ በማንሳት የበላይነቱን ይዘዋል። በአውሮፓ መድረክ ሪያል ማድሪድ 15 ጊዜ የሻምፒዮንስ ሊጉን ዋንጫ ከፍ በማድረግ ስኬታማ መሆን የቻለ ክለብ ነው። ጁቬንቱስ ሁለት ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አንስቷል። የእግር ኳስ ባለሙያዎች ከወቅታዊ ብቃት አንጻር ሪያል ማድሪድ ጁቬንቱስን በጠባብ የግብ ልዩነት ሊያሸንፍ ይችላል የሚል ግምታቸውን አስቀምጠዋል። በጥሎ ማለፍ የመጨረሻ መርሃ ግብር ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ከሞንቴሬይ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በሜርሴዲስ ቤንዝ ስታዲየም ይጫወታሉ።   ቦሩሲያ ዶርትሙንድ በሰባት ነጥብ የምድብ ስድስት መሪ፣ ሞንቴሬይ በምድብ አምስት በአምስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዘው ጥሎ ማለፍ ገብተዋል። ሁለቱ ክለቦች እርስ በእርስ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የሁለቱ ጨዋታ አሸናፊዎች በሩብ ፍጻሜው ይገናኛሉ። በአሜሪካ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ ፒኤስጂ፣ ባየር ሙኒክ፣ ቼልሲ፣ ፓልሜራስ፣ አል ሂላል እና ፍሉሜኔንሴ እስከ አሁን ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀሉ ክለቦች ናቸው።
አል ሂላል ማንችስተር ሲቲን በማሸነፍ ባልተጠበቀ ሁኔታ ወደ ሩብ ፍጻሜ ገብቷል
Jul 1, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፦ በፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ማለፍ መርሃ ግብር አል ሂላል ማንችስተር ሲቲን 4 ለ 3 አሸንፏል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በካምፒንግ ወርልድ ስታዲየም ተካሄዷል። ትናንት ከእኩለ ሌሊት በኋላ ጀምሮ እስከ ዛሬ ማለዳ በዘለቀው ጨዋታ በርናንዶ ሲልቫ በዘጠነኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ሲቲን መሪ አድርጓል። ማርኮስ ሊኦኖርዶ በ46ኛው እና ማልኮም በ56ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ባሳረፏቸው ግቦች አል ሂላልን መሪ ሆኗል። ኤርሊንግ ሃላንድ በ55ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ ቡዱኑን አቻ አድርጓል። ቡድኖቹ በመደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በመለያየታቸው ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ አምርተዋል። በተጨማሪ ሰዓት ካሊዶ ኩሊባሊ በ94ኛው ደቂቃ አል ሂላልን መልሶ መሪ ቢያደርግም ፊል ፎደን በ104ኛው ደቂቃ ማንችስተር ሲቲን በድጋሚ አቻ እንዲሆን አስችሏል። ማርኮስ ሊኦናርዶ በ112ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠራት ጎል አል ሂላልን ወደ ሩብ ፍጻሜ ልኳል። ልብ አንጠልጣይ ፋክክር በተደረገበት ጨዋታ የአል ሂላል የአልሸነፍ ባይነት ጽናት ባለድል አድርጓታል። ሁለት ግቦቹን ያስቆጠረው ማርኮስ ሊኦናርዶ የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተመርጧል። የአል ሂላል ግብ ጠባቂ ያሲን ቦኖ 10 ኳሶችን በማዳን ቡድኑን በጨዋታው እንዲቆይ በማድረግ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። የሳዑዲ አረቢያው ቡድን የአውሮፓውን ክለብ በማሸነፍ ዓለም ያልጠበቀውን ውጤት አስመዝገቧል። አል ሂላል በሩብ ፍጻሜው ከፍሉሜኔንሴ ጋር የፊታችን አርብ ይጫወታል። ፍሉሜኔንሴ ትናንት ኢንተር ሚላንን 2 ለ 0 አሸንፏል።
ፍሉሜኔንሴ ኢንተር ሚላንን በማሸነፍ ለሩብ ፍጻሜ አለፈ
Jul 1, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፦ በፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ማለፍ መርሃ ግብር ፍሉሜኔንሴ ኢንተር ሚላንን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በባንክ ኦፍ አሜሪካ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አርጀንቲናዊው አጥቂ ጀርመን ካኖ ጨዋታው በተጀመረ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል የብራዚሉን ቡድን መሪ አድርጓል። ብራዚላዊው የአማካይ ተጫዋች ሄርኩሊስ በ94ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል የቡድኑን አሸናፊነት አረጋግጧል። በጨዋታው ኢንተር ሚላን በኳስ ቁጥጥር የተሻለ የነበረው ቢሆንም የፍሉሜኔንሴን አይበገሬ የተከላካይ ክፍል ሰብሮ መግባት አልቻለም። ውጤቱን ተከትሎ ፍሉሜኔንሴ ለሩብ ፍጻሜው ያለፈ አምስተኛ ቡድን ሆኗል። የደቡብ አሜሪካው ክለብ የአውሮፓውን ክለብ አሸንፏል። ፍሉሜኔንሴ በሩብ ፍጻሜው ከማንችስተር ሲቲ እና አል ሂላል አሸናፊ ጋር ይጫወታል። ማንችስተር ሲቲ ከአል ሂላል በካምፒንግ ወርልድ ስታዲየም ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ ሁለት የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ  
Jun 30, 2025 99
  አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፦ በፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ የሶስተኛ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ምሽት 4 ሰዓት ላይ ኢንተር ሚላን ከፍሉሜኔንሴ በባንክ ኦፍ አሜሪካ ስታዲየም ይጫወታሉ። የዘንድሮው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ተፈላሚ የነበረው ኢንተር ሚላን በምድብ አምስት በሰባት ነጥብ የምድቡ መሪ በመሆን ማጠናቀቀቁ የሚታወስ ነው። ፍሉሜኔንሴ በምድብ ስድስት በአምስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ጥሎ ማለፉ ገብቷል። ሁለቱ ክለቦች ከዚህ ቀደም እርስ በእርስ ተገናኝተው አያውቁም። ጨዋታው በኢንተር ሚላን የማጥቃት አቅም እና የፍሉሜኔንሴ አይበገሬ የተከላካይ ክፍል መካከል የሚደረግ ጦርነት የሚል ስያሜ አግኝቷል።   በዓለም ዋንጫው በሶስት ጨዋታዎች ሁለት ግቦችን ያስቆጠረው የ27 ዓመቱ የኢንተር ሚላን አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ እና የ40 የፍሉሜኔንሴ አንጋፋ ተከላካይ ቲያጎ ሲልቫ የሚኖራቸው ፍጥጫ ይጠበቃል። ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በካምፒንግ ወርልድ ስታዲየም ማንችስተር ሲቲ ከአል ሂላል ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በምድብ ሰባት የነበረው ማንችስተር ሲቲ በዘጠኝ ነጥብ ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱ ይታወቃል። ሰማያዊዎቹ በውድድሩ የምድቡን ሁሉንም ጨዋታ ያሸነፈ ብቸኛ ክለብ ነው። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ጁቬንቱስን 5 ለ 2 ሲያሸንፍ ያሳየው ድንቅ ብቃት የዋንጫ ተገማችነቱን የበለጠ አሳድጎታል።   የሳዑዲ አረቢያው አል ሂላል በምድብ ስምንት ሪያል ማድሪድን ተከትሎ በአምስት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅሏል። ሁለቱ ክለቦች እ.አ.አ በ2012 በቅድመ ውድድር የወዳጅነት ጨዋታ ላይ ተገናኝተው አል-ሂላል 1 ለ 0 አሸንፏል። ማንችስተር ሲቲ ጨዋታውን የማሸነፍ ትልቅ ግምት ቢያገኝም ከተጋጣሚው ብርቱ ፉክክር ይጠብቀዋል። የጨዋታዎቹ አሸናፊዎች በሩብ ፍጻሜው የሚጫወቱ ይሆናል። በአሜሪካ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ ዛሬ 17ኛ ቀኑን ይዟል።
አካባቢ ጥበቃ
ባህር ዳር ከተማን ይበልጥ ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Jul 1, 2025 55
ባህርዳር ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፡- የባህር ዳር ከተማን ይበልጥ ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት በሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ተጠናክረው መቀጠላቸውን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ። "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ የባህር ዳር ከተማ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ማስጀመረያ የንቅናቄ መረሃ-ግብር ዛሬ ተካሂዷል። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው በመርሃ ግብሩ ላይ እንዳሉት ፤ ባህር ዳር ፅዱ ፣አረንጓዴና ደን የተጎናጸፈች ውብ ከተማ ናት። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብሮች የተተከለው ችግኝ የጽድቀት መጠንን በማሳደግ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን አውስተዋል።   ከተማዋ በጣና ሀይቅና በዓባይ ወንዝ የተከበበች መሆኗን በመጠቀም በአረንጓዴ ልማት ለኑሮና ለቱሪስት የተመቸች ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ባህር ዳርን ይበልጥ ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት በሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ገልጸዋል። የከተማ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ የሰው ዘር ደመላሽ በበኩላቸው፤ በባህር ዳር በክረምቱ ከ492 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ችግኝ ለመትከል ዝግጅት ተደርጎ ወደ ተግባር መገባቱን አስታውቀዋል። ከተዘጋጀው ችግኝ ውስጥም 45 በመቶ ለምግብነት የሚያገለግል አቡካዶ፣ ማንጎ፣ ሙዝ፣ ፓፓያና ሌላም የፍራፍሬ ችግኝ መሆኑን አመላክተዋል።   የችግኝ ተከላውን ለማሳካትም ጉድጓድ መዘጋጀቱን ጠቁመው፤ ለተከላ ከተለየው መሬት ውስጥም ከ199 ሄክታሩ ካርታ ተሰርቶለታል ብለዋል። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ሙሉጌታ ዳኛው በሰጡት አስተያየት፤ ችግኝ ለማንም ተብሎ ሳይሆን ለራስና ለልጅ ልጅ የሚተርፍ ጥቅም ያለው መሆኑን በማመን ዛሬ መትከል መጀመራቸውን ተናግረዋል። የሚተከለውን ችግኝም ከአካባቢያቸው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ተንከባክበው ለማሳደግ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል።   የአረንጓዴ ልማት ላይ በራሳቸው ተነሳሽነት እየተሳተፉ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ወይዘሮ አበባ ሀይሉ ናቸው።   በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የግብርና ባለሙያዎችና የከተማዋ ነዋሪዎች በአዲስ ዓለም ሆስፒታል ግቢ ውስጥ ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል።
የአረንጓዴ አሻራ ልማት ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ባለፈ የምግብ ዋስትና መሰረት ሆኖ እንዲዘልቅ እየተሰራ ነው
Jul 1, 2025 50
አምቦ፤ ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተፈጥሮ ሃብት ልማት ባለፈ የምግብ ዋስትና መሰረት ሆኖ እንዲዘልቅ እየተሰራ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ ገለጹ። የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ በመገኘት የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስጀምረዋል። ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ቀደም ሲል ዝግጅት መደረጉን አንስተው ችግኞች ለተከላ ዝግጁ በመሆናቸው ሁሉም አሻራውን እንዲያኖር አስገንዝበዋል።   በክልሉ ከዚህ በፊት የተተከሉ ችግኞች ለምተው ጥቅም በመስጠት ላይ መሆናቸውን አንስተው በቀጣይም ለደን ልማት፣ ለምግብነት የሚውሉ እና ለውበት የሚያገለግሉ ችግኞች የሚተከሉ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም ለዚህ መርሃ ግብር መሳካት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል አሻራውን ለማኖር የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። የምዕራብ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዲዳ ጉደታ፤ ለችግኝ ተከላው በተመረጡ አካባቢዎች ጎድጓዶች ተቆፍረው ዝግጁ መደረጋቸውን አንስተው ሁላችንም በመትከል አሻራችንን እናኑር ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።   በዞኑ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የምግብ ዋስትና እና ለደን ልማት የሚሆኑ ችግኞች መዘጋጀታቸውን አንስተዋል።
ትውልዱ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ለሀገር በጎ አሻራውን ሊያኖር ይገባል - ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
Jul 1, 2025 71
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ ትውልዱ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ለሀገር በጎ አሻራውን ሊያኖር ይገባል ሲሉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ-ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ ገለጹ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ-ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ፣ የቤተክርስቲያኗ አባቶች እና የከተማዋ አመራሮች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።   ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሀገርና በከተማ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመከላከል ለዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማይተካ ሚና እየተጫወተ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያንም ከጥንት ጀምሮ በገዳማትና አድባራት ችግኞችን በመትከል ለመጠለያነት፣ ለደከማቸው ማረፊያና ለትውልድ ማስተማሪያነት እየተጠቀመች ነው ብለዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን በመትከል የመንከባከብ ስራ ከቤተክርስቲያኗ ገዳማትና አድባራት ታሪክ ጋር ጥብቅ ትስስር ያለወ በጎ ተግባር መሆኑንም ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለተሻለ ሀገር ግንባታ ጉልህ ሚና ያለው በመሆኑ ትውልዱ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ በጎ ተግባርን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስና ከቤተ-ክርስቲያኗ አባቶች ጋር የአረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል ብለዋል። አረንጓዴ አሻራ የሁሉም ዜጋ የጋራ የልማት አጀንዳ ነው ያሉት ምክትል ከንቲባው፥ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በመርሃ ግብሩ ችግኝ የመትከል ስራውን አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።   የአዲስ አበባ የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ግርማ ሰይፉ በበኩላቸው በመዲናዋ 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ችግኞችን መትከል የሚያስችል መርሃ ግብር በይፋ መጀመሩን አውስተዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እና ብጹዓን አባቶች ያካሄዱት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርም ለትውልዱ ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል።   በቤተ-ክርስቲያኗ የፕሮጀክት መምሪያ ኃላፊ መላዕከ ህይወት ቆሞስ አባ ወልደየሱስ ሰይፉም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአየር ንብረት ደህንነትን የመጠበቅ እና የበረከት ሥራ ነው ብለዋል። ቤተክርስቲያኗም በመርሃ ግብሩ ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ አርዓያነቷን እንደምታስቀጥል ጠቁመዋል።   የቅኔና የመጽሐፍት ትርጓሜ መምህር ሊቀ-ጉባኤያት አባ ተክለሃይማኖት ወልዱ በበኩላቸው ችግኞችን መትከልና ተንከባክቦ ለፍሬ ማብቃት ከሁላችንም ይጠበቃል ነው ያሉት። ብፁዓን አባቶች በስፍራው ተገኝተው ያካሄዱት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሁሉም ዜጋ አርዓያ በመሆን ቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ሀገር እንዲረከብ ለማድረግ ፋይዳ እንዳለውም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዘንድሮውን 7 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞች የመትከል ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት አካባቢ ማስጀመራቸው ይታወቃል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የከተማዋን ገፅታ ቀይሯል - የአዳማ ከተማ ከንቲባ
Jul 1, 2025 81
አዳማ/ጅማ ፤ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ)፡-የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የከተማዋን ገፅታ መቀየሩን የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገለጹ። በከተማዋ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሄዷል። የችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩን ያስጀመሩት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሀይሉ ጀልዴ እንዳሉት የተፈጥሮ ሃብት መመናመንን ለመከላከል የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።   ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በከተማ አስተዳደሩ የተተከሉ ችግኞች የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ የገቢ ምንጭ በመሆን ጥቅም እያሰገኙ ነው ብለዋል። በዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም በ14 ተፋሰሶች ላይ 120 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስፍራን ለማልማት ታቅዶ ዛሬ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ መገባቱን ገልጸዋል። ከዚህም ባሻገር በትምህርትና በጤና ተቋማት እንዲሁም በወል መሬትና የኮሪደር ልማት በሚካሄድባቸውና በሌሎችም ስፍራዎች የችግኝ ተከላው በስፋት እንደሚካሄድ አውስተዋል። የአዳማ ከተማ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ቂልጡ በበኩላቸው በከተማዋ ለፍራፍሬና ለዛፍ የሚውሉ ችግኞች እንደሚተከሉ ተናግረዋል።   ለችግኝ ተከላው የቦታ መረጣና ጉድጓድ ዝግጅት ከማድረግ ባለፈ ህብረተሰቡ በበጎ ፈቃድ ለማሳተፍ ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል። በአዳማ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ላይ ችግኝ ሲተክሉ ያገኘናቸው አባገዳ መግራ ለገሰ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት በረሃማነትን ለመከላከል አረንጓዴ አሻራ ጉልህ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል።   የተራቆተ አካባቢን አረንጓዴ ለማልበስ የችግኝ ተከላው ወሳኝ በመሆኑ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ የዜግነት ግዴታቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። ሌላው የአዳማ ነዋሪ አቶ ግርማ ቶሌራ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የአካባቢያችንን ገጽታ ከመመለስ ባለፈ ለከተማዋ ውበት አሻራ የሚጥል ነው ብለዋል። በተመሳሳይም የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በዛሬው ዕለት በከተማዋ የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን አስጀምረዋል።   የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥሪ በመቀበል የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ለተከታታይ ስድስት አመታት ችግኝ መተከሉን ጠቁመዋል። በክረምት ችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ በ12 የችግኝ ጣቢያዎች ለምግብነት የሚውሉ ፍራፍሬዎችና እና ለዛፍ ጥላ የሚያገለግሉ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።   በጅማ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ከተሳተፉት መካከል አቶ ነጂብ አለሙ በየዓመቱ በሚደረገው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር መሳተፋቸውን ተናግረው መትከል ብቻም ሳይሆን መንከባከብ እንደሚገባም አመልክተዋል።  
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 503
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ።   በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1078
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል።   የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 772
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል።   ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1392
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 232
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል።   ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል።   የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው።   የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው።   ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።    
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 798
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች።   የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች።   ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ።   ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።      
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 911
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ቱሪዝሟ እያደገ የመጣው፣በባህላዊ ምግቦቿ እና ቡናዋ ዓለም አቀፍ እውቅና የተቸራት ኢትዮጵያ
May 11, 2025 738
በባህላዊ ታሪኳ እና ልዩ በሆኑ የምግብ አዘገጃጀቶች የምትታወቀው ኢትዮጵያ የበለጠ የዓለምን ትኩረት እየሳበች ትገኛለች። የናይጄሪያው ቢዝነስ ደይ ጋዜጣ ጋዜጠኛ ቺሶም ማይክል በጋዜጣው ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ብዙዎች በአፍሪካ ምርጡ ምግብ እና በዓለም ላይ ምርጡ ቡና ብለው የሚናገርላት ሀገር ብትሆንም አገሪቷ አሁንም ከሌሎች የአህጉሪቱ መዳረሻዎች ጋር ስትነጻጸር በአንፃራዊነት ጥቂት ቱሪስቶችን የምታስተናግድ ሀገር እንደሆነች ይገልጻል። ሞሮኮ እ.አ.አ በ2024 17 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቱሪስቶችን ስትቀበል ኬንያ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ጎብኚዎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያም የበርካታ ቱሪስቶች መዳረሻ የመሆን ጊዜዋ እየመጣ ይመስላል። የተባበሩት መንግስታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት (ዩኤንደብሊውቲኦ) በቅርቡ ባወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው እስከ 2024 ባለው አምስት ዓመት ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ አለም አቀፍ ቱሪስቶች በ40 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። 54ቱንም የአፍሪካ ሀገራት የጎበኙ አንድ ተጓዥ ኢትዮጵያን ሁለተኛ የቱሪዝም ተመራጭ አድርገውታል። "ለዚች ሀገር በጣም የተለየ ነገር ነው ያለኝ ብዙ ጥሩ የተፈጥሮ ቦታዎች አሏት" ብሏል። ይህም የኢትዮጵያ መንግስት ቱሪዝምን የኢኮኖሚያዊ እድገት ቁልፍ አካል ለማድረግ ያሳየው ቁርጠኝነት እንደሆነ ጋዜጠኛው ይገልጻል። በዩቲዩብ ላይ ከ5 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያለው የቱሪዝም ይዘት ላይ ድሪው ቢንስኪ ይህንኑ ሀሳብ ይጋራል። “ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ምርጥ ምግብ አላት። እንጀራ በጣም ጣፋጭ ነው በዓለም ሌላ ቦታ እንደዚህ ያለ ምግብ የለም። በአፍሪካ ምርጥ ምግብ፣ በዓለም ምርጥ ቡና ያለው እዚህ ሀገር ነው።” "እንጀራ ከጤፍ የተሰራ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ምግብ ውስጥ በጣም ዋና አካል ነው። እንጀራው ከብዙ ምግቦች እና ቅመሞች ጋር ይቀርባል።" ሲል ገልጿል። ኢትዮጵያዊያን የሚታወቁት በምግብ እና ቡና ብቻ አይደለም። ቱሪስቶች በኢትዮጵያ የተፈጥሮ እና ታሪካዊ መዳረሻዎች በጣም ይማረካሉ። በድንጋይ ከተቀረጹ የላሊበላ ውቅር አብያተ ቤተክርስቲያናት በጣም የሚጎበኙ የቱሪዝም መስህብ ነው። በጥልቅ ስምጥ ሸለቆ የታጀበው የሰሜን ተራሮች ለሰዎች ምቹ የእረፍት ጊዜ የሚሰጡ ናቸው። መዲናዋ አዲስ አበባ የባህል እና የምግብ ሁነቶች ማዕከል ናት። የኢትዮጵያ የቱሪዝም ልማት አካሄድ ቅርስ፣ መልክዐ ምድሮች እና ባህላዊ ልምዶችን ጨምሮ የተለያዩ መዳረሻዎችን ማስተዋወቅ ላይ ያተኮረ ነው። ካላት የቱሪዝም መዳረሻ አንጻር በኢትዮጵያ ብዙ ጎብኚዎች ባይኖሩም ያሏትን እድሎች በማስተዋወቅ ተደራሽነቷን እያሰፋች ነው። ልዩ ማንነት ያለው እና ጥልቅ ታሪክ ያላትን ኢትዮጵያን መጎብኘት ለሚሹ ሰፊ የቱሪዝም እድሎችን የምታቀርብ ሀገር ናት ይላል ጋዜጠኛው። በኢትዮጵያ ቱሪዝም እየጨመረ ብዙ ጎብኚዎች በምግቧ፣ ቡናዋ እና ታሪካዊ መዳረሻዎቿ እየተሳቡ ነው። በኢትዮጵያ ባህል እና የምግብ አሰራር ከዕለት ተዕለት የዜጎች ህይወት የተቆራኘባት ሀገር ናት። ኢትዮጵያ የተለየ ነገር ማቅረቧን ቀጥላለች። የቱሪዝም ሀብቶቿ ገና ያልተነካ ነው ኢትዮጵያ የወደፊት የዘርፉ እድገት አቅም ትልቅ ነው በማለት ጋዜጠኛ ቺሶም ጽሁፉን ቋጭቷል።  
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 2987
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 2531
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 2752
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 3873
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2316
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2180
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3616
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 47922
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43425
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 27854
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25199
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 23453
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 21631
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 21441
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 21076
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 47922
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43425
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 27854
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25199
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የዋጋ ንረት ምን ማለት ነው?
Jun 30, 2025 116
የዋጋ ንረት በንፅፅር ለምሳሌ አምና 26 በመቶ ዘንድሮ 14 በመቶ ሲሆን ምን ማለት ነው? ለምሳሌ የአንድን የ100 ብር ዕቃ ወስደን ብንመለከት ካቻምና ከነበረበት 100 ብር አምና 126 ብር ሆኖ ነበር ማለት ነው። ስለዚህ የዕቃው ዋጋ በአመት ብር 26 ጨምሯል ማለት ነው። በተመሳሳይ መንገድ አምና 100 ብር ዋጋ ያለው ዕቃ ዘንድሮ 14 በመቶ ካደገ ዘንድሮ 114 ብር ይሆናል ማለት ነው። በዚህ ስሌት የዕቃው ዋጋ ካምና ወደ ዘንድሮ የጨመረው በ14 ብር በመሆኑ አምና ከጨመረበት ብር 26 ጋር ሲነፃፀር ጭማሪው ቀንሷል ማለት ነው። ዋጋን ያየን እንደሆነ ግን 100 ብር የነበረ ዕቃ 114 በመሆኑ ጨመረ እንጂ አልቀነሰም። የዋጋ ንረት ጨመረ የሚባለው ደግሞ ለምሳሌ አምና 26 በመቶ የጨመረው ዘንድሮ 14 በመቶ ሳይሆን 30 በመቶ ቢሆን የጨመረው አምና 100 ብር የነበረው ዕቃ ዘንድሮ 114 ሳይሆን 130 ብር ይሆናል ማለት ነው። ይህ አምና ከጨመረበት የ26 ብር ይበልጣል ማለት ነው። ስለዚህ ካቻምና 100 ብር የነበረው ዕቃ አምና 26 ብር ጨምሮ 126 ከሆነ በኋላ ዘንድሮም 14 ብር ስለጨመረ በቀላል ቀመር ዘንድሮ 140 ብር ሆኗል ማለት ነው። ስለዚህ በሁለት አመታት የዕቃው ዋጋ 40 ብር ጨምሯል። የዕቃው ዋጋ አልቀነሰም በየአመቱ የጨመረበት ምጣኔ ግን ካምና ዘንድሮ ያነሰ ነው። ይህ ነው የዋጋ ንረት ቀነሰ ማለት። ዋጋ ቀነሰ ማለትስ ምን ማለት ነው? ዋጋ ቀነሰ የሚለውን ከማየት በፊት የዋጋ ንረት የለም ማለት ምን እንደሆነ በዛው 100 ብር ዋጋ ባለው ዕቃ እንመልከት። ይህ ባለፈው አመት ብር 100 የነበረ ዕቃ ዘንድሮም እዛው 100 ብር ላይ ቢቆይ የዋጋ ንረት ዜሮ ነው። ስለዚህ የዕቃው ዋጋ አልተለወጠም ማለት ነው። ዋጋ ቀነሰ ማለት ግን የዋጋ ንረት ከዜሮ በታች ይሆናል ማለት ነው። በምሳሌው ለማስረዳት አምና 100 ብር ዋጋ ያለው ዕቃ ዘንድሮ 90 ብር ቢሆን የዋጋ ንረቱ ወይም ለውጡ ከዜሮ በታች 10 በመቶ ነው። በዚህ ግዜ የዋጋ ንረት ቀነሰ ሳይሆን ዋጋ ቀነሰ ይባላል። እነዚህ ሶስቱ የዋጋ ለውጦች ለሸማቾችና ለአምራቾች ምን ማለት ናቸው? ለሸማቾች ከሁሉም የሚመረጠው ዋጋ ሲቀንስ ማለትም 100 ብር የነበረው ዕቃ 90 ብር ሲሆን ነው። በሁለተኛ ደረጃ ተመራጩ ዋጋ ንረት ሳይኖር አምና 100 ብር የነበረው ዕቃ ዘንድሮም ሳይለወጥ በዜሮ ንረት 100 ብር ላይ ሲቆይ ነው። ሶስተኛው የተሻለ አማራጭ አምና 100 ብር የነበረ ዕቃ ዘንድሮ በ26 በመቶ ጨምሮ ብር 126 ከሚሆን በ14 በመቶ ጨምሮ ብር 114 ሲሆን ነው። ይህ ሶሰተኛው አማራጭ በሁለቱም ዋጋ ስለሚጨምር በትንሽ የጨመረው ተመራጭ ይሆናል ማለት ነው። ከአምራቾች አንፃር ሲታይ ከላይ ለሸማቾች የተሻለ አማራጭ በቅደም ተከተል ያስቀምጥነውን ገልብጠው ማንበብ ነው። አሁን ብሔራዊ ባንክ እያለ ያለው የዋጋ ንረት ወይም አመታዊ ጭማሪው ቢበዛ ከ10 በመቶ እንዳይበልጥ የሚረዳ የገንዘብ ፖሊሲ እተገብራለሁ ነው። የባንኩ አላማ የዋጋ ንረት ዜሮ ወይም ከዜሮ በታች እንዲሆን ሳይሆን 1) ከ10 በመቶ በታች እንዲሆን ሲሆን 2) የትረጋጋና ተገማች እንዲሆን ነው። የተረጋጋ ማለት ከወር ወር ወይም ካመት አመት ዋጋ የሚለወጥበት ሁኔታ በጣም የተራራቀ ያልሆነ ማለት ነው። ለምሳሌ ካንዱ ወር ወደ ቀጣይ ወር ጭማሪው 0.5 በመቶ ሆኖ በቀጣይ ወር ደግሞ የ5 በመቶ ጭማሪ ከዚያም በቀጣይ ወር ከዜሮ በታች የ2 በመቶ ወርሃዊ ለውጥ ቢመዘገብ ያልተረጋጋ ወይም ተገማች ያልሆነ የዋጋ ለውጥ አለ ማለት ነው። ሰለዚህ የተረጋጋና ተገማች የዋጋ ለውጥ እንዲኖር ማድረግ የባንኩ ሁለተኛው አላማ ነው ማለት ነው። ብሔራዊ ባንክ በጣም ዝቅተኛ የዋጋ ንረት ወይም ከዜሮ በታች የዋጋ ለውጥ እንዴት ያየዋል ብለን ያየን እንደሆነ ነገሩ እንዲህ ነው። ቅድም ከላይ እንዳየነው የዋጋ ንረት ከሸማቾችና ካአምራቾች አንፃር የሚታየው በተቃራኒ መንገድ ነው። ስለሆነም ምንም እንኳን የዋጋ ንረት በጣም ዝቅተኛ ወይም ከዜሮ በታች ቢሆን ለሸማቾች ጥሩ ቢሆንም አምራቾችን ግን የማያበረታታ ስለሚሆን ማምረት ያቆማሉ ሠራተኛ ይቀንሳሉ አጠቃላይ የኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ይገታና ጭራሽ ከምርት እጥረት የተነሳ የዕቃዎች ዋጋ መናር ይከሰታል ሥራ አጥነት ይበዛል። ስለዚህ መንግስት ሥራ እንዲፈጠር ኢኮኖሚ እንዲነቃቃም ስለሚፈለግ የተረጋጋና ዝቅተኛ ሸማቹን የማይጎዳ አምራቹንም የሚያበረታተ የዋጋ ሁኔታ እንዲኖር ይሰራል ማለት ነው። ለአንድ ኢኮኖሚ ትክክለኛው የዋጋ ንረት ስንት ነው? ይህ ጥያቄ ሊመለስ የሚገባው ግን ከባድ ነው። ይህን ጥያቄ ለመመለለስ ከሚረዱት ሁኔታዎች አንዱ ኢኮኖሚው ያለበት ደረጃ ነው። ምን ማለት ነው በጣም ባደገና የበለጠ የማደግ እድሉ ጠባብ ለሆነ ኢኮኖሚ 1 በመቶ ወይም 2 በመቶ የዋጋ ንረት ከፍተኛ ሊሆን ይችላል። በአንፃሩ ደግሞ ገና የማደግ እምቅ አቅም ላለውና በማደግ ላይ ላለ ሀገር ነጠላ አሃዝ የዋጋ ንረት እንደ ሁኔታው የሚለያይ ሆኖ ተመራጭ ሊሆን ይችላል። ስንት ነው የሚለው ግን በሳይንሳዊ መንገድ መረጋገጥ አለበት። ለምሳሌ የሀገራችንን threshold inflation or optimal inflation level ለማወቅ እኔን ጨምሮ የባንኩ ሠራተኞች በሳይንሳዊ መንገድ ለማወቅ ተሞክሯል። በኔ ጥናት 7 በመቶ ሲሆን በሌሎቹም ከዚሁ ያልራቀ ውጤት እንዳለ አይቻለው የመረጃ አጠቃቀምና የሜቶዶሎጂ ልዩነቱ እንዳለ ሆኖ ማለቴ ነው። ሰለዚህ በነዚህ ጥናት መሰረት ብሔራዊ ባንክ የነጠላ አሃዝ የዋጋ ንረት አላማ አድርጎ መንቀሳቀሱ ትክክለኛ አቅጣጫ ነው ማለት ነው ለኛ ኢኮኖሚ። ለማጠቃለል የዋጋ ንረት ምንነትን በተመለከተ ያለውን ውዥምብር ለማጥራት ይህ አጭር መግለጫ ያግዛል ብዬ እያመንኩ የበለጠ መብራራት ካለበት ወይም ጥያቄ ካለ አንባቢዎች በአስተያየት መስጫው ላይ ማሰቀመጥ ትችላላችሁ። አቶ ፈቃዱ ደግፌ የብሔራዊ ባንክ ም/ገዥ
የሺህ ሀይቆች ምድር
Jun 24, 2025 408
የሺህ ሀይቆች ምድር (በራሔል አበበ) በርካታ መገለጫዎች አሏት። የሺህ ሀይቆች መፍለቂያ። አረንጓዴ ምድር። 75 በመቶ የአገሪቱ ገፀ-ምድር በደን የተሸፈነ። የአምስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ሕዝብ መኖሪያ። በአውሮፓ ከበለጸጉ አገራት አንዷ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለስምንት ተከታታይ ዓመታት በዓለም ቁጥር አንድ የደስተኞች አገር በመባል የተሰየመች ሰሜን አውሮፓዊት አገር - ፊንላንድ። በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋባዥነት በአዲስ አበባ የአገሪቱ ኤምባሲ አስተባባሪነት በቅርቡ ፊንላንድን የመጎብኘት ዕድል አግኝቼ ነበር። በጉብኝቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ የኬኒያ፣ ታንዛኒያ፣ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴኔጋል፤ ሞዛምቢክ እና ዛምቢያ ጋዜጠኞች ተሳትፈናል። የአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ ነው። ምንም እንኳን የትም አገር ስሄድ ቀድሜ መረጃ የማየት ልምድ ቢኖረኝም በመጀመሪያው ዕለት ለእራት ስንወጣ ያየሁት በምሽት ያልተለመደ የፀሐይ ፍካት ግን እራቱ ቁርስ እንዲመስለኝ አድርጓል። ከዚያ በኋላ ለመድሁት። በእርግጥ በአንድ ወቅት በስፔንም ፀሐይ እስከ እኩለ ሌሊት የማትጠልቅበትን ክስተት ተመልክቻለሁ። በፊንላንድ ያየሁት ግን ተለየብኝ። ፀሐይ ፈጽሞ ለጨረቃ ቦታ መልቀቅ አትፈልግም። ምሽቱ የሚደምቀው በመብራት ሳይሆን በፀሐይ ነው። ሌሊቱ ብርሀን ነው። ሰማይ አይጠቁርም። በየዕለቱ ሳይጨልም ይነጋል። በዚህ ወቅት በተለያዩ የአውሮፓና የአሜሪካ አገራት ሰማይ ላይ የሚታየው ሰሜናዊ የቀለማት የብርሀን ፀዳል ሌላው የፊንላንድ መድመቂያ ነው። የሰሜን አውሮፓ/ኖርዲክ አገራት በተፈጥሮ የታደሉ ናቸው። እኔ ደግሞ የተፈጥሮ አድናቂ ነኝ። ያለማጋነን በፊንላንድ ተፈጥሮ ከነክብሯ ተጠብቃ አይቻለሁ። ንጹህ አየሯ የዚህ ውጤት ነው። አድናቆቴ የጀመረው ከኤርፖርት እስካረፍኩበት ሆቴል 15 ኪሎ ሜትር ያህል በመኪና ስንጓዝ የከተማዋን አረንጓዴነትና የምድሪቱን ልምላሜ ስመለከት ነበር። በጉብኝቴም በተግባር አረጋገጥሁ። የአገሪቱ አብዛኛው መሬት በደንና በውሃ ተሸፍኗል። በዋና ከተማዋ ሄልሲንኪና በዙሪያዋ በሚገኙ ውብ ደኖች መሀል ስንጓዝ መሬቱ ለም ስለመሆኑ ዓይን ብቻ ሳይሆን እግርም ምስክር ነው። ሲራመዱ የመሬቱ ምቾትና እንደ ስፖንጅ ስምጥ ስምጥ ማለት ለምነቱን ይናገራል። በሄልሲንኪ ሴኔት እና ካንሳላስቶሪ አደባባዮች እንደእኛዎቹ አራት እና ስድስት ኪሎ አደባባዮች ናቸው። ቤተ-መንግስት፣ ዩኒቨርሲቲ፣ ፓርላማ፣ ቤተ-መጽሐፍት እና ቤተክርስቲያንን አጎራብተው ይዘዋል። የሄልሲንኪ ሕንጻዎች እንደ ሌሎች የአውሮፓ አገራት ውብና የሥነ-ሕንጻ ጥበብ የሚታይባቸው ናቸው። የነዋሪዎች ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ ከተማዋ አልተጨናነቀችም። በአስፋልትና ደረጃውን በጠበቀ ኮብልስቶን የተሰራው የከተማዋ አውራ ጎዳና ከዘመናዊ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ የህዝብ አውቶቡስና የኤሌክትሪክ ባቡር ያስተናግዳል። ለአውሮፓ ከተሞች አዲስ የሆነ ሰው ኮብልስቶኑ የእግረኛ መንገድ መስሎት መሐል የመኪና መንገድ ላይ ሊገኝ ይችላል። እኔም የተረፍሁት እንዲህ አይነቱን የመኪና መንገድ በአንድ ወቅት በኢጣልያ በማየቴ ነበር። የተፈጥሮ ውበት ደምቆ የሚታይባት ፊልናልድ ሲልቨር በርች የተሰኘው ብርማ ቀለም ቅርፊት ያለው ዛፍ እና ቡናማ ድብ ብሔራዊ መለያዎቿ ናቸው። በረጃጅሞቹ ዛፎች መሐል ከእንስሳት ባሻገር ስትሮበሪና እንጉዳይን ጨምሮ ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ዕጽዋት ይገኛሉ። በፊንላንድ ብዙ አይነት የእንጆሪ/ስትሮበሪ ዝርያ አለ። ወቅቱ ፍሬ የሚደርስበት አልነበረም እንጂ ከጫካዎቹ መሐል ገብቶ በተለያዩ የስትሮበሪ ፍሬዎች ቅርጫት ሞልቶ መውጣት የተለመደ መሆኑን ተረድቻለሁ። ፊንላንድ የሺህ ሀይቆች ምድር ተብላም ትሞካሻለች። ለቁጥር የሚያዳግቱ በበርካታ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሀይቆችና የውሀ አካላት ከተፈጥሮ ሀብቶቿ መካከል ናቸው። ለጉብኝት በሄድኩባቸው አካባቢዎች ሁሉ የሚቀርብልኝን ኩልል ያለ ንጹህ የመጠጥ ውሃ በፍቅር ነበር የምጠጣው። ግዴታ ካልሆነ የፋብሪካ ውሃ በፊንላንድ ቦታ የለውም። ንጹህ የተፈጥሮ የምንጭ ውሃ ከቧንቧ ይቀዳል። ጽድት ከማለቱ ጣዕሙ። ፊኒሾች ለባህልና ቅርስ ትልቅ ቦታ አላቸው። በተለይ ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ቁርኝት አስገራሚ ነው። በአብዛኛው አፍሪካ ውስጥ የሚነገር አፈ-ታሪክና ተረት በፊንላንድም ከተፈጥሮ በተለይም ከዛፎችና ከእንስሳት ጋር ተያይዞ ሲተረትና የመድረሻቸው መነሻ እንደሆነ ሲነገር ተደንቄያለሁ። በጉብኝታችን በአንዱ ቀን ኑኪሲኦ ብሔራዊ ፓርክ ሄድን። ይህ ደግሞ እጅግ የተለየ ተፈጥሮን ማያ ስፍራ ነው። በረዣዥም ዛፎች መሐል ካደረግነው ጉዞ በኋላ የቀረበልን ባህላዊው የፊንላንድ የሳውና እና የዋና ግብዣ ነበር። ሳውና የፊንላንድ ባህል ነው። በእንግሊዝኛ ቋንቋ መዝገበ ቃላት ውስጥ ያለ የፊኒሽ ቃል “ሳውና” እንደሆነ ይነገራል። ዛሬ በዓለም ላይ በተለይም በባለኮከብ ሆቴሎች በስፋት የምናገኘው ሳውና መነሻው ፊንላንድ ናት። በርካታ የሳውና ስፍራዎች ከመኖራቸው የተነሳ የሳውና ቁጥር በአገሪቱ ከተመዘገቡ መኪኖች ቁጥር ይበልጣል ይባላል። ግብዣውን ሁላችንም በደስታ ነበር የተቀበልነው። በባህሉ መሰረት ሳውና ውስጥ በቅጠል እየተጠበጠብን ከፍተኛ ሙቀት ሲሰማን ከፊት ለፊት ባለው ቀዝቃዛ የተፈጥሮ ሀይቅ ውስጥ በመግባት ዋና የሚችል ዋኝቶ የማይችል ደግሞ በመነከር ሰውነቱን አቀዝቅዞ እንደገና ወደሳውናው ይመለሳል። የተለየ ነው።     የጉብኝቱ ዋና አስተባባሪ አና ላሚላ ትባላለች። የ35 ዓመት የስራ ልምድ ያላት ብስል ዲፕሎማት ናት። በተለያዩ አገራት ፊንላንድን ወክላ ሰርታለች። አሁንም በአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አምባሳደር ነች። ትክክለኛ የኮሙኒኬሽን ሰው ናት። አንቺ ያልኳት በአንቱታ ላርቃት ባለመፈለጌ ነው። ለነገሩ ስትታይም የ35 ዓመት ወጣት እንጂ የ35 ዓመት የስራ ልምድ ያላት አትመስልም። አንድ ቀን አን “መኮንን” በሚለው የአያቴ ስም እየጠራችኝ ስምሽ እኮ የፊኒሽ/የፊንላንድ ነው ይህን ታውቂያለሽ? ከእኛ ጋር ዝምድና ይኖርሽ ይሆን?" አለችኝ ፈገግ ብላ። "ኸረ በፍፁም ኢትዮጵያዊት ነኝ" አልኳት። ትክክል ነበረች። አጭር የፅሁፍ መልዕክት የመለዋወጥ ሀሳብን ለመጀመሪያ ጊዜ ለዓለም ያስተዋወቀው “ማቲ መኮንን” የተባለ ፊንላንዳዊ ኢንጂኒየር ነው። የቴክኖሎጂ ነገር ከተነሳ አብዛኞቻችን ከተንቀሳቃሽ ስልክ ጋር ስንተዋወቅ የያዝነው ኖኪያ የፊንላንድ ምርት ነው። የመኮንንን ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ በተንቀሳቃሽ ስልክ አማካኝነት ለዓለም ይፋ ያደረገውም ኖኪያ ነው። አሁንም ኖኪያ በኔትወርክ ዝርጋታ ጭምር እየሰራ ያለ ግዙፍ የቴሌኮም ተቋም ነው። ኢትዮጵያና ፊንላንድ የረዥም ዓመታት የሁለትዮሽ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው። ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸው 66 ዓመታትን ተሻግሯል። ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ከእርዳታና ትብብር ባሻገር በተለያየ መስክ በጋራ ትሰራለች። በጉብኝቴ ወቅት ያገኘኋቸው የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሌና ቫልቶነን ይህን ግንኙነት የማሳደግ ፍላጎት መኖሩን ነግረውኛል። ከንግድና ኢንቨስትመንት በተጨማሪ ኖኪያን ከመሰሉ ኩባንያዎች ጋር የሚደረግ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና በአገሪቱ ቴክኖሎጂ መዘመኑን የተረዳሁት በአገሪቱ ብሔራዊ የሚዲያ ተቋም ይሌ ያለማንም እርዳታ ዜና ቀርጾ የሚያሰራጭ ሰው አልባ ሮቦትድ የስቱዲዮ ቴክኖሎጂ ስመለከት ነበር። ፊንላንድ በትምሕርት ጥራትም ስሟ በቀዳሚነት ይነሳል። በአገሪቱ ከ800 በላይ፤ በመዲናዋ ደግሞ 40 የሚጠጉ ቤተ-መጻሕፍት አሉ። ከአገሪቱ ፓርላማ አቅራቢያ የሚገኘውና አገሬው የእኩልነት ተምሳሌት ነው የሚለው የሄልሲንኪ ግዙፉ ማዕከላዊ ቤተ-መጽሐፍት ኦዲ ይባላል። በውስጡ በርካታ አገልግሎቶችን ይዟል። ንባብ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ የባህልና ፈጠራ ታለንቶችን ያስተናግዳል። ከልጅ እስከ አዋቂ ለሁሉም ቦታ አለው።   ፊንላንድ ዜጎቿ በደስታ ግብር የሚከፍሉባት አገር መሆኗን የአገሪቱ የታክስ አስተዳደር ሲናገር በኩራት ነው። ግብር መሰወር፤ ክፈሉ ብሎ በየግዜው መቀስቀስን የመሳሰሉ ነገሮች እዛ ቦታ የላቸውም። የኩባንያም ሆነ የግለሰብ ግብር ከፋዮች በታማኝነት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በወቅቱ እንደሚወጡ አስተዳደሩ ይገልጻል። ይህም የዜጎች ፍላጎትን ለማሟላት በተሰራ ስራ የተፈጠረ መሆኑን የተመለከትኳቸው ተቋማት ሃላፊዎች ይገልጻሉ። ዜጎች በመንግስት ላይ ከፍተኛ እምነት አላቸው። በፊንላንድ የዜጎች ደስተኝነት የሰላምና ነጻነት መገለጫ እንደሆነ ምሁራኖቻቸው በጥናት ስራዎቻቸው ጭምር ይመሰክራሉ። የደስታቸው ምንጭ ነጻና ጥራት ያለው ትምሕርት፣ በአካባቢ ጥበቃ፤ በፍትህና እኩልነት፤ በበጎ አድራጎት ተግባር፤ የእናቶችና ህጻናት ጤናን ጨምሮ አርአያ የሚሆኑ ጠንካራ የማሕበራዊ ደህንነትና ትስስር ስራዎች የመጡ ውጤቶች እንደሆኑ ይገለጻሉ። በጾታ እኩልነት ሴቶች በሁሉም መስክ ጥሩ ስፍራ አላቸው። በፖለቲካውም ከወንዶች ተቀራራቢ ቦታ እንዳላቸው የአገሪቱን ፓርላማ ስንጎበኝ ተረድቻለሁ። ከ200 የምክር ቤት አባላት 91ዱ ሴቶች ናቸው። የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ፊንላንድ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደስተኛ አገራት ደረጃ ላይ ለስምንት ተከታታይ ዓመታት የከፍታ ስፍራዋን ሳትለቅ በቁጥር አንድ ላይ እንድትቆይ አድርጓታል። ዜጎቿ በቀጣዩ ዓመትም ለዘጠነኛ ጊዜ የዓለም የደስተኞች አገር ሆና ትቀጥላለች የሚል እምነት አላቸው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም