አርእስተ ዜና
ቼልሲ ለፍጻሜ አለፈ
Jul 9, 2025 38
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ቼልሲ ፍሉሜኔንሴን 2 ለ 0 አሸንፏል። በሜትላይፍ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በ የ60 ሚሊዮን ፓውንድ ፈራሚው ጆአኦ ፔድሮ በ18ኛው እና 56ኛው ደቂቃ ላይ በግሩም ሁኔታ ያስቆጠራቸው ግቦች ቡድኑን አሸናፊ አድርጓል። ፔድሮ የልጅነት ክለቡ ላይ ግቦቹን ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን በተቀዛቀዘ መልኩ ገልጿል። ጨዋታው ተመጣጣኝ እና ጠንካራ ፉክክር ተደርጎበታል። ቼልሲ ለግብ የቀረቡ እድሎችን በመፍጠር የተሻለ ነበር። ጠንካራው የፍሉሜንሴ የተከላካይ መስመር በጨዋታው ላይ ባልተለመደ ሁኔታ ስህተቶችን ሲሰራ ተስተውሏል። ቡድኑ ከ11 ጨዋታዎች በኋላ ሽንፈት አስተናግዷል። የቼልሲ የአማካይ ተጫዋች ሞሰስ ካሲዬዶ በጉዳት ምክንያት በጨዋታው ማብቂያ ላይ ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። ዋንጫውን ለማንሳት ከፒኤስጂ እና ሪያል ማድሪድ አሸናፊ ጋር ያደርጋል። ፒኤስጂ እና ሪያል ማድሪድ ነገ የሚያደርጉት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
በክልሉ ከ8 ሺህ በላይ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እና ጥገና ይከናወናል
Jul 8, 2025 79
ባህርዳር፤ ሐምሌ 1/2017 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ8 ሺህ በላይ የአቅመ ደካማ ቤቶችን የመገንባት እና የመጠገን ስራ እንደሚከናወን ተገለጸ። ክልላዊ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ በባህርዳር ከተማ ጣና ክፍለ ከተማ ዛሬ ተጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እንደገለጹት፤ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን እሴት መሰረት በማድረግ እየተከናወነ ይገኛል።   በጎ ፈቃደኞችም በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ፣ የአቅመ ደካሞችን መኖሪያ ቤት በመስራትና በመጠገን፣ የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት፣ የሰብል ልማትና ሌሎች ተግባራት ለማከናወን እንደተዘጋጁ አስታውቀዋል። በዚህም በክልል ደረጃ ከ8 ሺህ በላይ የአቅመ ደካሞችን መኖሪያ ቤት ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ በመገንባትና በመጠገን የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ ይደረጋል ብለዋል። ለዚህም የህዝብን አቅም ፣ የመንግስት እና የልማት ድርጅቶች ተሳትፎ በማጎልበት ተፈጻሚ እንደሚሆን ተናግረዋል። በሁሉም የክልሉ ዞኖች፣ የከተማ አተዳደሮችና ወረዳዎች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ዛሬ በይፋ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል። የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ የዳበረ ባህላዊ እሴታችን የሆነውን በጎነትን በመተግበር የብልፅግና ጉዞን እናረጋግጣለን ብለዋል።   የተጀመሩ ሰው ተኮር ስራዎችን በበጎ ፈቃድ ስራ በማጠናከር ወገኖችን መደገፍ ይገባናል ሲሉ አመልክተዋል። በከተማ አስተዳደሩ ባለፈው ዓመት የክረምት ወራት 375 የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶችን በመገንባትና በማደስ ለተጠቃሚዎች ማስረከብ መቻሉን አውስተዋል። በዘንድሮው ክረምትም ካለፈው ዓመት በተሻለ መልኩ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶችን ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ ገንብቶ ለማስረከብ በቂ ዝግጅት መደረጉንም አስታውቀዋል።   በክረምት በጎ ፈቃድ ክልላዊ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የሰሜን ጎጃም ዞንና የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።  
በአማራ ክልል ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት ይጠናከራሉ
Jul 8, 2025 66
ባሕርዳር ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የታክስ አስተዳደሩን በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓት በማዘመንና በማቀላጠፍ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚጠናከሩ ተገለጸ። የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ከሐምሌ ጀምሮ በየዓመቱ የሚካሄደውን የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች የንቅናቄ መድረክ ማምሻውን በባሕር ዳር ከተማ አካሄዷል።   በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ባደረጉት ንግግር፤ የክልሉን ልማት ለማፋጠን፣ ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈንና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም የታክስ አስተዳደሩን በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓት በማዘመን ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። ይህም አሰራሩን ቀልጣፋና ፍትሃዊ ማድረግ፣ የግብር ስወራን በመቆጣጠር፣ ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ግብር መረቡ ማስገባት ላይ የአዲሱ በጀት ዓመት ትኩረት መሆኑን ጠቅሰዋል። ለስኬታማነቱም በየደረጃው ያለው አመራር፣ የዘርፉ ባለሙያና ሌላው ባለድርሻ አካል በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ክብረት ማህሙድ በበኩላቸው፤ የክልሉ ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ ለልማት በማዋል በኩል ቀደም ሲል አበረታች ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል፡፡ በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከተለያዩ የገቢ አርዕስቶች 58 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ በክልሉ ለሚካሄዱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ማዋል መቻሉን ገልጸዋል። በተጀመረው አዲሱ የበጀት ዓመት በክልሉ የወጪ ፍላጎትን በራስ አቅም ለመሸፈን በገቢ አሰባሰቡ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ለዚህም አመራርና ባለሙያ እንዲሁም ግብር ግብር ከፋይ የሚጠበቅበትን በመክፈል ሁሉም ኃላፊነቱን በተገቢው ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በንቅናቄ መድረኩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬን ጨምሮ ሌሎች የስራ ሃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ግብርን በአግባቡ በመክፈል ለሀገር ልማትና እድገት የምናደርገውን አስተዋጽኦ እናጠናክራለን- የንግዱ ማህበረሰብ አባላት
Jul 8, 2025 68
ሐረር ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ግብርን በአግባቡ በመክፈል ለሀገር ልማትና እድገት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩ በሐረሪ ክልል የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተናገሩ። በሐረሪ ክልል ለታማኝና ከፍተኛ ግብር ከፋዮች እውቅና የመስጠት ስነ-ስርዓት ዛሬ ተካሄዷል።   በወቅቱም ታማኝና ከፍተኛ ግብር ከፋዮቹ እንደገለፁት፤ ግብርን በወቅቱና በአግባቡ በመክፈል ለሀገር ልማትና እድገት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ አጠናክረው ይቀጥላሉ።   በከተማው በዓይን ህክምና እና በሌሎች ኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩት ዶክተር ኑረዲን አብዲ እንዳሉት ህዝቡ ለሚያነሳው የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በግብር የሚሰበሰብ ገቢ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ግብር መክፈል “የውዴታ ግዴታ ነው” ያሉት ዶክተር ኑረዲን የተሻለች አገርን ለመገንባትና ለትውልድ ለማስተላለፍ ግብርን በወቅቱ መክፈል እንደሚገባና ለተሰጣቸውም እውቅና ምስጋና አቅርበዋል። ''ግብር የምንከፍለው ልማቱ ተሳልጦ የማህበረሰቡ ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ወሳኝ በመሆኑ ነው'' ያሉት ደግሞ በከተማው በሆቴል ስራ የተሰማሩት አቶ ወንድሙ ፈይሳ ናቸው።   ግብር በመክፈሌ የዜግነት ግዴታዬን ተወጥቻለሁ፤ በዚህም ሽልማት ተበርክቶልኛል፤ ሁሉም የሚጠበቅበትን ግብር በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታውን ሊወጣ ይገባል ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በከተማው በህክምና ሙያ ዘርፍ ላይ የተሰማሩት ዶክተር ኑረዲን አህመድ በበኩላቸው ግብርን በወቅቱ መክፈል የዜግነት ግዴታን ከመወጣት ባሻገር ለዜጎች የስራ እድልን ለመፍጠር ሚናው የጎላ በመሆኑ ሁሉም ሃላፊነቱን መወጣት አለበት ብለዋል።   በተያዘው በጀት ዓመት ከ4 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የክልሉን 63 በመቶ የልማት ወጪ የመሸፈን ስራ ለማከናወን ዕቅድ መያዙን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ያሲን አብዱላሂ ናቸው። በተለይ በክልሉ ግብርን በአግባቡ ለሚከፍሉ ታማኝ ግብር ከፋዮችም ምስጋና አቅርበዋል።     የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በክልሉ ግብር ከፋዩ ግብሩን በአግባቡ በመክፈል ግዴታውን እንዲወጣ አሳስበው ከታክስ ማጭበርበርና ግብር ስወራ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮችን በህግ አግባብ የመቅረፉ ተግባር ይጠናከራል ብለዋል።
የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ፕሮጀክት ነው
Jul 8, 2025 64
ሚዛን አማን፤ ሐምሌ 1/2017 (ኢዜአ)፡- የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ መገንባት የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ትልቅ ፕሮጀክት ነው ሲሉ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። የአውሮፕላን ማረፊያው የግንባታ ሥራ ያለበትን ደረጃ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በስፍራው በመገኘት ተመልክተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦለት እየተገነባ ያለው የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ የመንገዱ ሥራው ከ1 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር በላይ አስፋልት ለብሷል።   በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሚዛን አማን ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ፕሮጀክቱ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በተመለከቱበት ወቅት እንደገለጹት፤ የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ በሕዝብ ጥያቄ መነሻ እየተገነባ ያለ ትልቅ ፕሮጀክት ነው። የአካባቢውን የቱሪዝም አቅም ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር ዘላቂ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።   ቡና እና ቅመማ ቅመምን ጨምሮ ሌሎችም ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የግብርና ምርቶችን የግብይት ሂደት ለማሳለጥ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነም ጠቅሰዋል።የግንባታ ሂደቱ ጥሩ ደረጃ ላይ መሆኑን መረዳታቸውን ገልጸዋል። በምልከታው የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል ፣ የክልል እና የዞን የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።  
የሚታይ
አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራን ማስፋት አለብን - የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ
Jul 8, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአህጉሪቷ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋት ሀገራት በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ፥ የስራ አጥነት ችግር የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአህጉሪቱ ፈተና መሆኑን አንስተዋል። የስራ አጥነት ችግርን ለማቃለል የአፍሪካ አገራት በጋራ በመስራት ከፍተኛ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ አንስተዋል። ስለሆነም አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የስራ ፈጠራን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር ላይ ትኩረት ተደርጎ መስራት እንደሚገባ አስታውቀዋል። ለዚህም ጥሬ ዕቃ መላክ ብቻ ሳይሆን ብዙ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ እሴት ጨማሪ የምርት ሰንሰለቶችን በመዘርጋት በዜጋ ተጠቃሚነትና በወጪ ንግድ ዕድገት ላይ ትኩረት ማድረግ የግድ ነው ብለዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ የፋይናንስ አካታችነት ስራዎችን በማሻሻልና የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣናን በመተግበር ተጨማሪ የሥራ ዕድሎችን መፍጠር አስፈላጊ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል። ዜጎች ለህገወጥ ስደት እንዳይዳረጉ፣ በሀገራቸው ሰርተው እንዲለወጡና ተከብረው እንዲኖሩ አህጉራዊ ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በስራ ገበያ መረጃ ስርዓት፣ በክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ እና በህጋዊ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝም አንስተዋል። በፎረሙ የፋይናንስ አካታችነት፣ የዲጂታልና የንግድ መሰረተ ልማቶች፣ የህግ ማዕቀፍ ክፍተቶች፣ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣና ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ጠቁመዋል።  
ኢትዮጵያ በሥራ ዕድል ፈጠራ ከአፍሪካ ሀገራትና ከአህጉራዊ ተቋማት ጋር ትብብሯን አጠናክራ ትቀጥላለች
Jul 8, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በክህሎት ልማት ዘርፍ ከአፍሪካ ሀገራትና ከአህጉራዊ ተቋማት ጋር ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል። ከፎረሙ በተጓዳኝ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ግሩፕ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።       የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚህ ወቅት እንደገለጹት ኢትዮጵያ ለወጣቶች የክህሎት ልማት እና የሥራ ዕድል ፈጠራ አበክራ እየሰራች ትገኛለች። በአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራን ተቋማዊ አድርጎ ከመተግበርና አሰራርን ከማመቻቸት አንጻር የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያም በክህሎት ልማት፣ በሥራ ገበያና መሰል ጉዳዮች ከአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ጋር ባለፉት ሶስት ዓመታት በጋራ ስትሰራ ቆይታለች ነው ያሉት።   በዛሬው እለት የተደረገው የመግባቢያ ስምምነትም ከድርጅቱ ጋር የሚሰሩ ስራዎችን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እና አህጉራዊ ትብብርን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ድርጅቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ቀጣናዊ ጽህፈት ቤት መክፈቱን ገልጸው፤ ይህም ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትስስር በማሳደግ በኩል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉዓለም ስዩም በበኩላቸው ተቋሙ በአፍሪካ ቀጣይነት ያለው የስራ እድል ፈጠራን ለማጎልበት እየሰራ ነው ብለዋል።   ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር የተደረገው ስምምነት በኢትዮጵያ የስራ እድል ፈጠራን ዘላቂነት ባለው መልኩ ለማስፋፋት የሚከናወኑ ስራዎች ላይ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል። በፋይናንስ ዘርፍና የገበያ ትስስር መፍጠር ስራዎች ላይ የተቀናጀ ድጋፍ በማድረግ የንግድ ድርጅቶችን አቅምና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ድጋፍ እንደሚያደርግም አብራርተዋል።
በክልሉ የፍራፍሬ እና የደን ችግኞችን በግል ማሳና የወል መሬት ላይ በማልማት ለዘላቂ ተጠቃሚነት መትጋት ይገባል
Jul 8, 2025 68
ባሕርዳር፤ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የፍራፍሬ ፣ የደን እና የእንስሳት መኖ ችግኞችን በግል ማሳና በወል መሬት ላይ በመትከልና በማልማት ለዘላቂ ተጠቃሚነት መትጋት እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ አሳሰቡ። "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ በአቦላ ተራራ ተፋሰስ ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ተጀምሯል።   የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በመርሃ ግብሩ ባደረጉት ንግግር፤ ችግሮችን የምንሻገረው የተራቆቱ አካባቢዎችን በችግኝ ተከላ አረንጓዴ በማልበስ ሁለንተናዊ ልማትን ማፋጠን ስንችል ነው ብለዋል። ችግኝ በመትከል የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቋቋም ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚቻል ህዝቡ ተገንዝቦ ለአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ሙሉ አቅሙን ተጠቅመን መስራት አለብን ሲሉ ገልጸዋል። የተተከለውን ተንከባክቦ ማሳደግ የሁሉም ኃላፊነት መሆን እንዳለበትም አመልክተዋል። በመርሃ ግብሩም የፍራፍሬ፣ የደንና የእንስሳት መኖ ችግኞችን በግል ማሳና በወል መሬት ላይ በመትከልና በማልማት ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መትጋት እንደሚገባ ገልጸዋል። በየደረጃው የሚገኘው አመራርና የዘርፉ ባለሙያም ሳይንሳዊ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን ለማስፈፀም ሊረባረቡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የግብርና ሚኒስቴር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና ሌሎች የግብርና ስራዎች እያደረገ ያለው ድጋፍ ያመሰገኑት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በቀጣይም እገዛውን አጠናክሮ እንዲቀጠልም አመልክተዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤልያስ በበኩላቸው፤ የደን ሀብትን ጠብቆ ይበልጥ ለማሳደግ የተጀመረው ችግኝ ተከላ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   ባለፉት ሰባት ዓመታት እንደሀገር በአረንጓዴ አሻራ የተተከለው ችግኝ የፅድቀት ምጣኔውም 80 በመቶ ማድረስ መቻሉን አረጋግጠዋል። ዛሬ በአማራ ክልል ይልማና ዴንሳ ወረዳ በአቦላ ተራራ ተፋሰስ የተተከለው ችግኝም የአካባቢው ሕብረተሰብ የቱሩፋቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ተንከባክቦ እንዲያሳድግ መልእክት አስተላልፈዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ክላስተር ዘርፍ አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር ) ፤ በክልሉ ሁሉም አካባቢ ዛሬ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በይፋ መጀመሩን አስታውቀዋል።   ለችግኝ ተከላውም 1 ነጥብ 55 ቢሊዮን ችግኝ መዘጋጀቱን ጠቅሰው፤ ከዚህም ውስጥ 20 ሚሊዮን የሚሆነው ቡናን ጨምሮ የተለያዩ ፍራፍሬዎች እንደሆኑ ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች የክልሉን መልካም ገፅታ ይበልጥ ከማጉላት ባሻገር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት በማሳደግ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል። ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል፣ የክልልና የዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።  
የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ ፈጠራ የተሞላበት የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መጠቀም ይገባል -የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ
Jul 8, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ ፈጠራ የተሞላበት የቴክኖሎጂ ውጤቶች መጠቀም እንደሚገባ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ። ቱሪዝም ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በሀገራችን የሚገኙ መዳረሻዎችን እና የቱሪዝም አገልግሎቶችን በተሻለ ሁኔታ በማስተዋወቅ “ቪዚት ኢትዮጵያ" የተሰኘ ሀገር በቀል የግብይት ድረገፅ በይፋ ስራ ጀምሯል። ቪዚት ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዕምቅ ሀብት፣ የቱሪዝም መዳረሻዎች ለአለም የሚያስተዋውቅ ድረገፅ መሆኑ ተገልጿል።   በይፋ ማድረጊያ መርሃግብሩ ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሀሚድ፣ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የቪዚት ኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻዎችንና አገልግሎት ሰጪዎችን የሚያስተዋውቅ እንዲሁም ቻት ቦትን ያካተተ ነው ተብሏል።   በዚህ ወቅት የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እንዳሉት ኢትዮጵያ በርካታ የቱሪዝም ፀጋዎች አሏት። የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ ፈጠራ የተሞላበት የቴክኖሎጂ ውጤቶች መጠቀም ይገባል ብለዋል። ቪዚት ኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻዎችን የተመለከተ ወቅታዊና ጥራቱን የጠበቀ መረጃ ማቅረብ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል። የቱሪዝም ዘርፍ ተዋንያንን በአንድ በይነ መረብ የሚያስተሳስር ነው ብለዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሀሚድ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የበለፀገ የባህል ስብጥርና የቱሪዝም ሀብት ያላት አገር መሆኗንም ገልጸዋል።   ያለንበት የዲጂታል ዘመን ጎብኚዎች ባሉበት በመሆን ቪዚት ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፉን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉበት ነው ብለዋል። ቪዚት ኢትዮጵያ ደህንነቱ የተጠበቀና ተጠቃሚን ማዕከል ያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል የፈጠሩ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን እየተገበረች ነው
Jul 8, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም አካባቢ እያከናወነቻቸው ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል እየፈጠሩ መሆኑን መገንዘባቸውን የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ተሳታፊዎች ገለጹ። በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው ሦስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም በአህጉሪቱ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም ለአፍሪካውያን ወጣቶች የሥራ እድል ለመፍጠር ትብብርን የሚያጎለብት እንደሆነ ተሳታፊዎች ገልጸዋል። ኡጋንዳዊው ተሳታፊ ናምጎ ጆብ እንደገለጸው፤ ፎረሙ በአፍሪካ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም በሥራ እድል ፈጠራ የተያዙ እቅዶችን በትብብር መተግበር ለአህጉሪቷ ወጣቶች ተስፋ የሚሰጥ ነው። ይህም አፍሪካውያን ወጣቶች በአገራቸው ሰርተው የመበልጸግ ርዕያቸውን እውን በማድረግ ከስደት እንደሚታደጋቸው ገልጿል። ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አዲስ አበባ የመጣው እ.ኤ.አ በ2023 እንደነበር በማስታወስ፤ አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ሲመጣ የአዲስ አበባ የመሰረተ ልማት መስፋፋትና የከተማዋ እድገት እንዳስገረመውም ጠቅሷል። የአዲስ አበባ ዘመናዊ መሰረተ ልማት፣ የከተማ ውበት፣ የጎዳናዎች ስፋትና ጽዳት "በአፍሪካ የአውሮፓ ከተማ ውስጥ እንዳለሁ ተሰምቶኛል" ሲል የከተማዋን ዕድገት አድንቋል። በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል የሚፈጥሩ መሆኑን መገንዘቡን በማንሳት፥ ኢትዮጵያ በብሩህ ተስፋ ጉዞ ላይ ናት ብለዋል። በኮሜሳ የሴት ነጋዴዎች ማህበር ፌዴሬሽን የቦርድ ሊቀ መንበር ሞሪን ሶቦይ ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡበት ወቅት የሚያገኙት አዳዲስ ለውጥ ሀገሪቱ በፈጣን እድገት ላይ መሆኗን የሚያመላክት እንደሆነ ገልጸዋል።   ሌሎች የአፍሪካ አገራትም ከኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ልምድ ሊወስዱ እንደሚገባ ጠቁመዋል። አዲስ አበባ በከተማ ውበት፣ እድገትና ጽዱ አካባቢን በመፍጠር እያሳየች ያለው ለውጥም ለመኖሪያ ምቹ ያደርጋታል ነው ያሉት። በኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ የስራ ድርጅት ዋና የቴክኒክ አማካሪ አንቶኒ አይንታ ኢትዮጵያ ለራሷ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት አገሮችም አቅም መሆን የሚችል ብቁ የሰው ሃይል አላት ብለዋል።   አህጉሪቱን በንግድና አገልግሎት ለማስተሳሰር ከተያዘው ራዕይ ጎን ለጎን በሰለጠነ የሰው ሃይል የወጣቶችን እውቀት በመጠቀም በስራ ፈጠራ ማስተሳሰር እንደሚቻል ጨምረዋል። ሦስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም የግብርና እሴት ሰንሰለት፣ ዲጂታላይዜሽንና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ አስተማማኝ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር ላይ ምክክር በማድረግ ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በምግብ ራስን ለመቻል በሚደረገው ጥረት ኮሞሮስ ከኢትዮጵያ ብዙ ልምድ መውሰድ ትችላለች-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ
Jul 8, 2025 97
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦በምግብ ራስን ለመቻል በሚደረገው ጥረት ኮሞሮስ ከኢትዮጵያ ብዙ ልምድ መውሰድ ትችላለች ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ተናገሩ። ኮሞሮስ ባቀረበችው ግብዣ መሰረት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ 50ኛው የኮሞሮስ የነፃነት በዓል በሞሮኒ ከተማ ሲከበር መታደማቸው የሚታወስ ነው፡፡ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ከኮሞሮስ ለቀረበላቸው ግብዣ ምስጋና አቅርበው፥ ኢትዮጵያ ከኮሞሮስ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገር ፍላጎት እንዳላት አብራርተዋል፡፡ ከ120 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ያላት ኢትዮጵያ በምግብ ምርት ራሷን ለመቻል ባደረገችው ጥረት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቷንም አስገንዝበዋል።   ፕሬዝዳንቱ አክለውም፥ ኮሞሮስ በግብርናው ዘርፍ ከኢትዮጵያ ትልቅ ተሞክሮ ልትወስድ እንደምትችል አስረድተዋል፡፡ የኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ በበኩላቸው፥ የፕሬዝዳንት ታዬ በዚህ በዓል ላይ መገኘት ኢትዮጵያ ለኮሞሮስ ያላትን ክብር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ፥ ከፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይትን ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።፡ በውይይታቸው ወቅትም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ማዕከል መሆኗንም ገልጸዋል፡፡ ፕሬዝዳንት አዛሊ ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለው ኢኮኖሚያዊ ለውጥ አፍሪካውያንን ለተሻለ እድገት የሚያነሳሳ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡   የኢትዮጵያ ለውጥ ማሳያ የሆነውን የኢትዮጵያ አየር መንገድም ኮሞሮስን ከተቀረው አፍሪካ እና አለም ጋር በማገናኘት ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ የኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ፥ ከኢትዮጵያ ስንዴ የመግዛት ፍላጎት እንዳላትም ተናግረዋል፡፡
ስሎቬኒያ ከኢትዮጵያ ጋር በፖለቲካ እና ኢኮኖሚው መስክ ያላትን ትብብር ማጠናከር ትሻለች - አምባሳደር ክሪስቲና ራዴጅ
Jul 8, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ ስሎቬኒያ ከኢትዮጵያ ጋር በፖለቲካ እና ኢኮኖሚው መስክ ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻ በኢትዮጵያ የስሎቬኒያ አምባሳደር ክሪስቲና ራዴጅ ገለጹ። ስሎቬኒያ እ.አ.አ ኖቬምበር 1/2024 በአዲስ አበባ ኤምባሲዋን መክፈቷ ይታወቃል። በኢትዮጵያ የስሎቬኒያ አምባሳደር ክሪስቲና ራዴጅ የኤምባሲው መከፈት ስሎቬኒያ ከኢትዮጵያ እና አፍሪካ ጋር ያላትን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትብብር ለማጎልበት ያላትን ስትራቴጂካዊ ቁርጠኝነት የሚያመላክት መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲሎማሲ ማዕከል ናት ያሉት አምባሳደሯ ኤምባሲው ስሎቬኒያ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ለማጠናከር እና ለባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ስራዎች እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ስሎቬኒያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከርና በቀጣናዊ ትስስርና የድህረ ግጭት መልሶ ማቋቋምና መልሶ ግንባታ ላይ ያላትን ልምድ ማካፈል እንደምትፈልግ ተናግረዋል። በኢኮኖሚ እና ንግድ መስክ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሻም ነው የገለጹት። ግብርና፣ ታዳሽ ኃይልና ቴክኖሎጂ ስሎቬኒያ ከለየቻቸው የልማት መስኮች መካከል እንደሚጠቀሱ ገልጸው የስሎቬኒያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያሉ እድሎችን ለመመልከት የቅደመ-ኢንቨስትመንት ጉብኝቶች ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። ስሎቬኒያ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በግብርና ኢኖቬሽን ውጤቶች ላይ ያላትን ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ማጋራት እንደምትፈልግም አምባሳደሯ ገልጸዋል። እንደ አምባሳደሯ ገለጻ፤ ስሎቬኒያ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች አርሶ አደሮችና በግብርና ምርቶች ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎችን በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በሙከራ ደረጃ ላይ የሚገኙ የንብ ማነብ ስራ ፕሮግራሞችን እየደገፈች ነው። እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያ እና ስሎቬኒያ የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ሀገራቸው ቁርጠኛ እንደሆነችም አመልክተዋል። ስሎቬኒያ የአፍሪካን የቅድሚያ ትኩረቶች መሰረት ባደረገ መልኩ የአህጉሪቱ ትልሞች እንዲሳኩ ድጋፍ ማድረግ እንደምትፈልግ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ስሎቬኒያ በግንቦት ወር 2017 ዓ.ም ሶስተኛ የፖለቲካ ምክክራቸውን በአዲስ አበባ ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን በምክክሩም ሀገራቱ ያላቸውን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብር ለማጠናከር ተስማማተዋል። የስሎቬኒያ ፕሬዝዳንት ናታሻ ፒርች ሙሳር በግንቦት ወር 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ያደረጉት ይፋዊ የስራ ጉብኝት የትብብሩ እያደገ መምጣት ማሳያ ነው።
የአውሮፓ ህብረት አፍሪካ መር የሰላም ማስፈን ጥረቶችን እንደሚደግፍ ገለጸ
Jul 8, 2025 117
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር ሰላም እና እርቅን ለማምጣት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አስታወቀ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከአውሮፓ ህብረት የሳሄል ልዩ ተወካይ ጆአ ክራቪንሆ እና ከህብረቱ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ተወካይ አኔት ዌበር (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።   ሁለቱ ወገኖች እየተለወጠ በመጣው የሳሄል ቀጣና እና የአፍሪካ ተለዋዋጭ የደህንነት ሁኔታዎች ላይ የሀሳብ ልውውጥ አድርገዋል። የቀጣናው ችግሮች ቀጣናዊ መፍትሄዎች እንዲያገኙ የማድረግ ጥረትን በተቀናጀ የባለብዝሃ ወገን የተግባር ምላሽ መደገፍ እንደሚገባም አንስተዋል።   የአውሮፓ ህብረት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ግጭትን በመከላከል ዲፕሎማሲ (preventive diplomacy) ያላቸውን ጠንካራ አመራር ሰጪነት አድንቀዋል። የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ህብረት መር አህጉራዊ የእርቅ፣ የማረጋጋት እና የግጭት መፍታት ጥረቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ እንደሆነ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶች ሀገራት ኢትዮጵያ በስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ያላትን ፍላጎት እና አቋም እንዲረዱ ያስቻለ ነው - ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር)
Jul 7, 2025 174
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30 /2017(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከ17ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከሀገራት መሪዎች ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ኢትዮጵያ በስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ያላትን ፍላጎትና አቋም እንዲረዱና እንዲደግፉ ያስቻለ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ገለጹ። በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ እየተካሄደ ባለው 17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው ተሳትፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) 17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ከጉባኤው ጎን ለጎን ከሀገራት መሪዎች ጋር የተደረጉ ውይይቶች የሁለትዮሽ ትብብርን ለማጠናከርና የሀሳብ ልውውጥ ለማድረግ ያስቻለ መልካም አጋጣሚ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በተለያዩ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ያላትን ፍላጎትና አቋም ሀገራቱ እንዲረዱና እንዲደግፉ ለማግባባት ጥሩ እድል መፍጠሩንም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከብራዚል ፕሬዝዳንት ኢግናሲዮ ሉላ ዳሲልቫ ጋር ባደረጉት ውይይት የሁለትዮሽ በተለይም የኢኮኖሚ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሀሳብ መለዋወጣቸውን አመልክተዋል። ውይይቱ የብራዚሉ ፕሬዝዳንት የኢትዮጵያን አቅጣጫ እና ፖሊሲ በአግባቡ እንዲረዱ ለማድረግ ጥሩ እድል መፍጠሩንም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ ጋር የሁለቱን ሀገራት ጠንካራ ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም ጠቅሰዋል። የኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት ትብብሩን ማጠናከር በውይይቱ አጽንኦት የተሰጠው ጉዳይ እንደሆነም ገልጸዋል። ቻይና በኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ዘርፍ ያላትን አዎንታዊ አስተዋጽኦ የምታጠናክርበትን ሁኔታ በፓሪስ ክለብ ማዕቀፍ ውስጥ ቻይና ከፈረንሳይ ጋር በመሆን የኢትዮጵያ እዳ ላይ ሽግሽግ እንዲደረግ የተወጣችውን ከፍተኛ ሚና አጠናክራ ማስቀጠል በምትችልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከራቸውን አንስተዋል። ቻይና በቅርቡ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት ከቀረጥ ነጻ ሸቀጥ ና ኤክስፖርት ማስገባት የሚችሉበትን መንገድ ማመቻቸቷና የሰጠችውን እድል አስመልክቶ የሀሳብ ልውውጥ መደረጉንም ሚኒስትሩ አንስተዋል። የቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ቡና ምርት በስፋት ወደ ቻይና እየገባ እንደሚገኝ ጠቅሰው የሀገራቱን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙንት ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ስሪል ራማፎሳ ጋርም የሁለትዮሽ ምክክር አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅን ለፕሬዝንዳቱ አብስረዋል ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በግድቡ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸውን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባል ሀገራት ልምድ፣ ቴክኖሎጂና ኢንቨስትመንት ማግኘት ትፈልጋለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቱ በትብብር ማዕቀፉ አስተዋጽኦ የምታበረክትባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸዋል። ውይይቶቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሀገራቱ ጋር ላለው ትብብር የሰጡትን ትኩረት እንደሚያመላክት ጠቅሰው ብሪክስ የጋራ ትብብርን ማጠናከር የሚያስችል ቁልፍ ማዕቀፍ እና አደረጃጀት መሆኑን አክለዋል።
በበጀት ዓመቱ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ የሚያስረዱና ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክሩ የፓርላማ ዲፕሎማሲ ሥራዎች ተከናውነዋል
Jul 7, 2025 130
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በ2017 በጀት ዓመት የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ የሚያስረዱና ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክሩ የፓርላማ ዲፕሎማሲ ሥራዎች መከናወናቸውን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ። ምክትል አፈ ጉባኤዋ ይህን ያሉት ምክር ቤቱ ባካሄደው 3ኛ ልዩ ስብሰባ ላይ የበጀት ዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሲያቀርቡ ነው። በዚሁ ወቅት በምክር ቤቱ ባሉ 16 የወዳጅነት ቡድኖች የተለያዩ የፓርላሜንታዊ ዲፕሎማሲ ሥራዎች መሰራታቸውን ነው ያብራሩት።   ከዚህ ውስጥ የምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች በጄኔቫ በተደረገ የዓለም ፓርላማ ኅብረት(IPU) ላይ መሳተፋቸውንና ከደቡብ ሱዳንና ናሚቢያ ከመጡ የፓርላማ አባላት ጋር የልምድ ልውውጥ መደረጉን ገልጸዋል። በኡጋንዳ በተካሄደ የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት የፓርላማ ትብብር ጉባኤ ላይ የተሳተፉ የቋሚ ኮሚቴ አባላት ኢትዮጵያ በግብርናና በምግብ ራስን ለመቻል እያደረገች ስላለው ስኬታማ ስራዎች ማስረዳታቸውን አንስተዋል። በቋሚ ኮሚቴ ደረጃና በወዳጅነት ቡድኖች ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ስራዎችን መሰራታቸውንም ተናግረዋል። በዚህም በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና ጤናን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የልምድ ልውውጦች መደረጋቸውን ነው ያነሱት። በበጀት ዓመቱ የኢትዮ-ፈረንሳይ፣ ኢትዮ-እስራኤል፣ ኢትዮ-አዘርባጃን፣ ኢትዮ-ደቡብ ኮሪያ፣ ኢትዮ-ጀርመን፣ ኢትዮ-ሞንጎሊያ፣ ኢትዮ-ኢራን፣ ኢትዮ-ፊንላንድ፣ ኢትዮ-ቻይና፣ የኢትዮ-ፓኪስታን፣ ኢትዮ-ካዛኪስታንና የኢትዮ-ስዊድን የወዳጅነት ቡድኖች ጋር ፍሬያማ ውይይቶች ተደርገዋል ብለዋል። ከኢትዮ-ግሪክ የወዳጅነት ቡድን አባላት ጋር በፓርላማ ዲፕሎማሲ፣ በቴክኖሎጂ፣ በባህር ትራንስፖርት፣ በቱሪዝምና ኮንስትራክሽን ዘርፍ አብሮ ለመሥራት ያለመ ውይይት መደረጉን አንስተዋል። በበጀት ዓመቱ በምክር ቤት ደረጃ 3 እና በቋሚ ኮሚቴዎች 22 በድምሩ 25 የፓርላማ ልዑካን ቡድን፣ የወዳጅነት ቡድን እና ሀገራት ጋር የጠንካራ ዲፕሎማሲ ሥራዎች መከናወናቸውን እንዲሁ።
ሕግ የማውጣት፣ የክትትልና የሕዝብ ውክልና ሥራዎች ምክር ቤቱ ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት መከናወኑን የመከታተል ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Jul 7, 2025 130
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ ሕግ የማውጣት፣ የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የውክልና ሥራዎች የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት መከናወናቸውን የመከታተል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። ምክር ቤቱ ባካሄደው 3ኛ ልዩ ስብሰባ ላይ የበጀት ዓመቱ የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።   ሪፖርቱን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ ባቀረቡበት ወቅት ምክር ቤቱ ባሉት አደረጃጀቶች በእቅድ የያዛቸውን ሥራዎች በብቃት ለመፈፀም በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። በተለይ ምክር ቤቱ በሕግ የተሰጠውን አራት ዋና ዋና ተልዕኮዎች ለማሳካት የሰራቸው ሥራዎች ውጤታማ ናቸው ብለዋል። ምክር ቤቱ በሕገ-መንግሥቱ በተሰጠው ሥልጣንና ተግባር መሠረት ሕግ የማውጣት፣ የፌዴራል አስፈፃሚ አካላትን የመከታተልና የመቆጣጠር፣ የሕዝብ ውክልና ሥራ እና የፓርላማ ዲፕሎማሲ ተግባራትን ትኩረት በመስጠት ማከናወኑን አብራርተዋል። ምክር ቤቱ ባሉት 13 ቋሚ ኮሚቴዎች በአስፈፃሚ አካላት እቅድ ላይ ክትትልና ድጋፍ ማድረጉንም በሪፖርቱ አንስተዋል። የምክር ቤቱ አባላት በዓመት ሁለት ጊዜ የሚያካሂዷቸው የምርጫ ክልል የውክልና ሥራም በአግባቡ እየተመራና ሕዝቡ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።   ሕጎች ከመፅደቃቸው በፊትም በየደረጃው ያሉ የምክር ቤቱ የሕግ ክፍል ባለሙያዎችና የቋሚ ኮሚቴ አባላት ዝርዝር ምርመራ እንደሚያደርጉበት አስታውቀዋል። ከዚህ ባለፈ የአስረጂና የሕዝብ ውይይት መድረኮችን በማመቻቸት በህጎቹ ላይ ግልፅነት እንዲፈጠር ተደርጓል ነው ያሉት። በበጀት ዓመቱ ምክር ቤቱ ባካሄዳቸው 43 መደበኛ እና ልዩ ስብሰባዎች ከ50 በላይ አዋጆችን መርምሮ ማፅደቁን ነው የገለፁት። ምክር ቤቱ በ2017 በጀት ዓመት ለሀገርና ሕዝብ ሁለንተናዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ሕጎች መርምሮ ማፅደቁን አብራርተዋል። የምክር ቤቱ አባላት በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ የተልዕኮ ስራዎች የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገባቸውን ገልጸዋል። ይሁንና ከውክልና ስራ ጋር ተያይዞ ህዝቡ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች ላይ አስፈጻሚ አካላት የእርምት እርምጃ ከመውሰድ ጋር ተያይዞ የሚታዩ ክፍተቶች በቀጣይ ዓመት በትኩረት ሊሰራባቸው ይገባል ብለዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ምክር ቤቱ የሚያወጣቸው ሕጎች በአግባቡ መፈፀማቸውን ኦዲት ማድረግ መጀመሩን አስታውቀዋል። የምክር ቤቱ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎችም በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሰረት እየተመሩና የተጠያቂነት አሰራርም ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ምክር ቤቱ ሕግ የማውጣት፣ የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የውክልና ሥራን ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት እንዲከናወን የማድረግ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ምክር ቤቱ በበጀት ዓመቱ በእቅድ የያዛቸውን ተግባራት ለማሳካት ያደረገው ርብርብ ውጤታማ እንደነበር ነው የገለጹት። በቀጣዩ በምክር ቤቱ አምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመን የነበሩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል ያጋጠሙ ክፍተቶችን በመሙላት የተሻለ ሥራ ለመከወን ሁሉም አባላት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ኢትዮጵያ በጉባኤው ላይ ብሄራዊ ጥቅሟንና የገለልተኝነት መርህን አማክላ አቋሟን በሚገባ አንጸባርቃለች- ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር)
Jul 7, 2025 169
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በ17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ብሄራዊ ጥቅሟንና የገለልተኝነት መርህን ማዕከል አድርጋ አቋሟን በሚገባ ማንጸባረቋን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። 17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ ተካሄዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው በጉባኤው ላይ ተሳትፈዋል። ሚኒስትሩ ጉባኤውን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ ሪዮ ዴጄኔሮ ያቀኑት በጉባኤው ላይ ለመሳተፍና ከሀገራት መሪዎች ጋር በመወያያት የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከርን ዓላማ በማድረግ መሆኑን ገልጸዋል። መሪዎቹ ከተወያዩባቸው አበይት አጀንዳዎች መካከል አካታች እና ፍትሃዊ የዓለም አስተዳደር ስርዓት እና ሪፎርም ይገኝበታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም እና የገለልተኝነት መርህን መሰረት በማድረግ ዓለም ሁሉንም አካባቢ ማቀፍ እንደሚገባው እና የአፍሪካ ድምጽ በሁሉም የዓለም ተቋማት እኩል መደመጥ እንዳለበት ማንሳታቸውን ነው ሚኒስትሩ የገለጹት። አፍሪካ ከመደመጥ ባሻገር ተሳትፎዋ ሊያድግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው መናገራቸውን አመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የደቡብ ለደቡብ ትብብርን ማጠናከርን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት የረጅም ጊዜ ስልጣኔ፣ ብዝሃ ባህል እና ታሪክ ያላት ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላትን የባህልና የኢኮኖሚ ትብብር ለማጠናከር እና ልምድ ለመቅሰም እንደምትሰራ ተናግረዋል። ከኢኮኖሚ እና ከፋይናንስ ጋር በተገናኘም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከብሪክስ ጋር ባላት ትብብር ተጠቃሚ እየሆነች እንደምትገኝ ገልጸዋል። የብሪክስ ልማት ባንክ አይነት የፋይናንስ ተቋም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ኢ-ፍትሃዊ የፋይናንስ እና የብድር አቅርቦት አማራጭ መሆናቸውንና ኢትዮጵያ ከዚህ ተጠቃሚ እንደምትሆን ነው ያነሱት። ዲጂታላዜሽን እና ሰው ሰራሽ አስተውሎትም ሌላኛው የውይይት ርዕሰ ጉዳይ ነበር። ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ዓለሙ ይዞ የመጣቸውን መልካም እድሎች የበለጠ መጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀነስ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ መናገራቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ሰፋፊ ስራዎችን እያከናወነች እንደምትገኝ እና በዘርፉ ከብሪክስ ሀገራት ጋር በትብብር መስራት እንደምትሻ ጠቅሰዋል። ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከንግግር ባለፈ በተግባር ለዓለም ምሳሌ የሚሆን ስራ እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል። ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በአጠቃላይ በብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ የተሳካ ተሳትፎ ማድረጓን ጠቁመዋል።
ፖለቲካ
በምግብ ራስን ለመቻል በሚደረገው ጥረት ኮሞሮስ ከኢትዮጵያ ብዙ ልምድ መውሰድ ትችላለች-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ
Jul 8, 2025 97
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦በምግብ ራስን ለመቻል በሚደረገው ጥረት ኮሞሮስ ከኢትዮጵያ ብዙ ልምድ መውሰድ ትችላለች ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ተናገሩ። ኮሞሮስ ባቀረበችው ግብዣ መሰረት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ 50ኛው የኮሞሮስ የነፃነት በዓል በሞሮኒ ከተማ ሲከበር መታደማቸው የሚታወስ ነው፡፡ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ከኮሞሮስ ለቀረበላቸው ግብዣ ምስጋና አቅርበው፥ ኢትዮጵያ ከኮሞሮስ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገር ፍላጎት እንዳላት አብራርተዋል፡፡ ከ120 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ያላት ኢትዮጵያ በምግብ ምርት ራሷን ለመቻል ባደረገችው ጥረት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቷንም አስገንዝበዋል።   ፕሬዝዳንቱ አክለውም፥ ኮሞሮስ በግብርናው ዘርፍ ከኢትዮጵያ ትልቅ ተሞክሮ ልትወስድ እንደምትችል አስረድተዋል፡፡ የኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ በበኩላቸው፥ የፕሬዝዳንት ታዬ በዚህ በዓል ላይ መገኘት ኢትዮጵያ ለኮሞሮስ ያላትን ክብር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ፥ ከፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይትን ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።፡ በውይይታቸው ወቅትም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ማዕከል መሆኗንም ገልጸዋል፡፡ ፕሬዝዳንት አዛሊ ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለው ኢኮኖሚያዊ ለውጥ አፍሪካውያንን ለተሻለ እድገት የሚያነሳሳ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡   የኢትዮጵያ ለውጥ ማሳያ የሆነውን የኢትዮጵያ አየር መንገድም ኮሞሮስን ከተቀረው አፍሪካ እና አለም ጋር በማገናኘት ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ የኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ፥ ከኢትዮጵያ ስንዴ የመግዛት ፍላጎት እንዳላትም ተናግረዋል፡፡
ስሎቬኒያ ከኢትዮጵያ ጋር በፖለቲካ እና ኢኮኖሚው መስክ ያላትን ትብብር ማጠናከር ትሻለች - አምባሳደር ክሪስቲና ራዴጅ
Jul 8, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ ስሎቬኒያ ከኢትዮጵያ ጋር በፖለቲካ እና ኢኮኖሚው መስክ ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻ በኢትዮጵያ የስሎቬኒያ አምባሳደር ክሪስቲና ራዴጅ ገለጹ። ስሎቬኒያ እ.አ.አ ኖቬምበር 1/2024 በአዲስ አበባ ኤምባሲዋን መክፈቷ ይታወቃል። በኢትዮጵያ የስሎቬኒያ አምባሳደር ክሪስቲና ራዴጅ የኤምባሲው መከፈት ስሎቬኒያ ከኢትዮጵያ እና አፍሪካ ጋር ያላትን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትብብር ለማጎልበት ያላትን ስትራቴጂካዊ ቁርጠኝነት የሚያመላክት መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲሎማሲ ማዕከል ናት ያሉት አምባሳደሯ ኤምባሲው ስሎቬኒያ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ለማጠናከር እና ለባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ ስራዎች እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ስሎቬኒያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከርና በቀጣናዊ ትስስርና የድህረ ግጭት መልሶ ማቋቋምና መልሶ ግንባታ ላይ ያላትን ልምድ ማካፈል እንደምትፈልግ ተናግረዋል። በኢኮኖሚ እና ንግድ መስክ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሻም ነው የገለጹት። ግብርና፣ ታዳሽ ኃይልና ቴክኖሎጂ ስሎቬኒያ ከለየቻቸው የልማት መስኮች መካከል እንደሚጠቀሱ ገልጸው የስሎቬኒያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያሉ እድሎችን ለመመልከት የቅደመ-ኢንቨስትመንት ጉብኝቶች ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። ስሎቬኒያ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በግብርና ኢኖቬሽን ውጤቶች ላይ ያላትን ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ማጋራት እንደምትፈልግም አምባሳደሯ ገልጸዋል። እንደ አምባሳደሯ ገለጻ፤ ስሎቬኒያ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች አርሶ አደሮችና በግብርና ምርቶች ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎችን በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በሙከራ ደረጃ ላይ የሚገኙ የንብ ማነብ ስራ ፕሮግራሞችን እየደገፈች ነው። እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያ እና ስሎቬኒያ የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ሀገራቸው ቁርጠኛ እንደሆነችም አመልክተዋል። ስሎቬኒያ የአፍሪካን የቅድሚያ ትኩረቶች መሰረት ባደረገ መልኩ የአህጉሪቱ ትልሞች እንዲሳኩ ድጋፍ ማድረግ እንደምትፈልግ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ስሎቬኒያ በግንቦት ወር 2017 ዓ.ም ሶስተኛ የፖለቲካ ምክክራቸውን በአዲስ አበባ ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን በምክክሩም ሀገራቱ ያላቸውን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብር ለማጠናከር ተስማማተዋል። የስሎቬኒያ ፕሬዝዳንት ናታሻ ፒርች ሙሳር በግንቦት ወር 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ያደረጉት ይፋዊ የስራ ጉብኝት የትብብሩ እያደገ መምጣት ማሳያ ነው።
የአውሮፓ ህብረት አፍሪካ መር የሰላም ማስፈን ጥረቶችን እንደሚደግፍ ገለጸ
Jul 8, 2025 117
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር ሰላም እና እርቅን ለማምጣት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አስታወቀ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከአውሮፓ ህብረት የሳሄል ልዩ ተወካይ ጆአ ክራቪንሆ እና ከህብረቱ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ተወካይ አኔት ዌበር (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።   ሁለቱ ወገኖች እየተለወጠ በመጣው የሳሄል ቀጣና እና የአፍሪካ ተለዋዋጭ የደህንነት ሁኔታዎች ላይ የሀሳብ ልውውጥ አድርገዋል። የቀጣናው ችግሮች ቀጣናዊ መፍትሄዎች እንዲያገኙ የማድረግ ጥረትን በተቀናጀ የባለብዝሃ ወገን የተግባር ምላሽ መደገፍ እንደሚገባም አንስተዋል።   የአውሮፓ ህብረት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ግጭትን በመከላከል ዲፕሎማሲ (preventive diplomacy) ያላቸውን ጠንካራ አመራር ሰጪነት አድንቀዋል። የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ህብረት መር አህጉራዊ የእርቅ፣ የማረጋጋት እና የግጭት መፍታት ጥረቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ እንደሆነ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶች ሀገራት ኢትዮጵያ በስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ያላትን ፍላጎት እና አቋም እንዲረዱ ያስቻለ ነው - ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር)
Jul 7, 2025 174
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30 /2017(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከ17ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከሀገራት መሪዎች ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ኢትዮጵያ በስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ያላትን ፍላጎትና አቋም እንዲረዱና እንዲደግፉ ያስቻለ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ገለጹ። በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ እየተካሄደ ባለው 17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው ተሳትፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) 17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ከጉባኤው ጎን ለጎን ከሀገራት መሪዎች ጋር የተደረጉ ውይይቶች የሁለትዮሽ ትብብርን ለማጠናከርና የሀሳብ ልውውጥ ለማድረግ ያስቻለ መልካም አጋጣሚ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በተለያዩ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ያላትን ፍላጎትና አቋም ሀገራቱ እንዲረዱና እንዲደግፉ ለማግባባት ጥሩ እድል መፍጠሩንም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከብራዚል ፕሬዝዳንት ኢግናሲዮ ሉላ ዳሲልቫ ጋር ባደረጉት ውይይት የሁለትዮሽ በተለይም የኢኮኖሚ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሀሳብ መለዋወጣቸውን አመልክተዋል። ውይይቱ የብራዚሉ ፕሬዝዳንት የኢትዮጵያን አቅጣጫ እና ፖሊሲ በአግባቡ እንዲረዱ ለማድረግ ጥሩ እድል መፍጠሩንም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ ጋር የሁለቱን ሀገራት ጠንካራ ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም ጠቅሰዋል። የኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት ትብብሩን ማጠናከር በውይይቱ አጽንኦት የተሰጠው ጉዳይ እንደሆነም ገልጸዋል። ቻይና በኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ዘርፍ ያላትን አዎንታዊ አስተዋጽኦ የምታጠናክርበትን ሁኔታ በፓሪስ ክለብ ማዕቀፍ ውስጥ ቻይና ከፈረንሳይ ጋር በመሆን የኢትዮጵያ እዳ ላይ ሽግሽግ እንዲደረግ የተወጣችውን ከፍተኛ ሚና አጠናክራ ማስቀጠል በምትችልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከራቸውን አንስተዋል። ቻይና በቅርቡ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት ከቀረጥ ነጻ ሸቀጥ ና ኤክስፖርት ማስገባት የሚችሉበትን መንገድ ማመቻቸቷና የሰጠችውን እድል አስመልክቶ የሀሳብ ልውውጥ መደረጉንም ሚኒስትሩ አንስተዋል። የቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ቡና ምርት በስፋት ወደ ቻይና እየገባ እንደሚገኝ ጠቅሰው የሀገራቱን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙንት ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ስሪል ራማፎሳ ጋርም የሁለትዮሽ ምክክር አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅን ለፕሬዝንዳቱ አብስረዋል ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በግድቡ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸውን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባል ሀገራት ልምድ፣ ቴክኖሎጂና ኢንቨስትመንት ማግኘት ትፈልጋለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቱ በትብብር ማዕቀፉ አስተዋጽኦ የምታበረክትባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸዋል። ውይይቶቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሀገራቱ ጋር ላለው ትብብር የሰጡትን ትኩረት እንደሚያመላክት ጠቅሰው ብሪክስ የጋራ ትብብርን ማጠናከር የሚያስችል ቁልፍ ማዕቀፍ እና አደረጃጀት መሆኑን አክለዋል።
በበጀት ዓመቱ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ የሚያስረዱና ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክሩ የፓርላማ ዲፕሎማሲ ሥራዎች ተከናውነዋል
Jul 7, 2025 130
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በ2017 በጀት ዓመት የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ የሚያስረዱና ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክሩ የፓርላማ ዲፕሎማሲ ሥራዎች መከናወናቸውን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ። ምክትል አፈ ጉባኤዋ ይህን ያሉት ምክር ቤቱ ባካሄደው 3ኛ ልዩ ስብሰባ ላይ የበጀት ዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሲያቀርቡ ነው። በዚሁ ወቅት በምክር ቤቱ ባሉ 16 የወዳጅነት ቡድኖች የተለያዩ የፓርላሜንታዊ ዲፕሎማሲ ሥራዎች መሰራታቸውን ነው ያብራሩት።   ከዚህ ውስጥ የምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች በጄኔቫ በተደረገ የዓለም ፓርላማ ኅብረት(IPU) ላይ መሳተፋቸውንና ከደቡብ ሱዳንና ናሚቢያ ከመጡ የፓርላማ አባላት ጋር የልምድ ልውውጥ መደረጉን ገልጸዋል። በኡጋንዳ በተካሄደ የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት የፓርላማ ትብብር ጉባኤ ላይ የተሳተፉ የቋሚ ኮሚቴ አባላት ኢትዮጵያ በግብርናና በምግብ ራስን ለመቻል እያደረገች ስላለው ስኬታማ ስራዎች ማስረዳታቸውን አንስተዋል። በቋሚ ኮሚቴ ደረጃና በወዳጅነት ቡድኖች ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ስራዎችን መሰራታቸውንም ተናግረዋል። በዚህም በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና ጤናን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የልምድ ልውውጦች መደረጋቸውን ነው ያነሱት። በበጀት ዓመቱ የኢትዮ-ፈረንሳይ፣ ኢትዮ-እስራኤል፣ ኢትዮ-አዘርባጃን፣ ኢትዮ-ደቡብ ኮሪያ፣ ኢትዮ-ጀርመን፣ ኢትዮ-ሞንጎሊያ፣ ኢትዮ-ኢራን፣ ኢትዮ-ፊንላንድ፣ ኢትዮ-ቻይና፣ የኢትዮ-ፓኪስታን፣ ኢትዮ-ካዛኪስታንና የኢትዮ-ስዊድን የወዳጅነት ቡድኖች ጋር ፍሬያማ ውይይቶች ተደርገዋል ብለዋል። ከኢትዮ-ግሪክ የወዳጅነት ቡድን አባላት ጋር በፓርላማ ዲፕሎማሲ፣ በቴክኖሎጂ፣ በባህር ትራንስፖርት፣ በቱሪዝምና ኮንስትራክሽን ዘርፍ አብሮ ለመሥራት ያለመ ውይይት መደረጉን አንስተዋል። በበጀት ዓመቱ በምክር ቤት ደረጃ 3 እና በቋሚ ኮሚቴዎች 22 በድምሩ 25 የፓርላማ ልዑካን ቡድን፣ የወዳጅነት ቡድን እና ሀገራት ጋር የጠንካራ ዲፕሎማሲ ሥራዎች መከናወናቸውን እንዲሁ።
ሕግ የማውጣት፣ የክትትልና የሕዝብ ውክልና ሥራዎች ምክር ቤቱ ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት መከናወኑን የመከታተል ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Jul 7, 2025 130
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ ሕግ የማውጣት፣ የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የውክልና ሥራዎች የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት መከናወናቸውን የመከታተል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። ምክር ቤቱ ባካሄደው 3ኛ ልዩ ስብሰባ ላይ የበጀት ዓመቱ የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።   ሪፖርቱን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ ባቀረቡበት ወቅት ምክር ቤቱ ባሉት አደረጃጀቶች በእቅድ የያዛቸውን ሥራዎች በብቃት ለመፈፀም በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። በተለይ ምክር ቤቱ በሕግ የተሰጠውን አራት ዋና ዋና ተልዕኮዎች ለማሳካት የሰራቸው ሥራዎች ውጤታማ ናቸው ብለዋል። ምክር ቤቱ በሕገ-መንግሥቱ በተሰጠው ሥልጣንና ተግባር መሠረት ሕግ የማውጣት፣ የፌዴራል አስፈፃሚ አካላትን የመከታተልና የመቆጣጠር፣ የሕዝብ ውክልና ሥራ እና የፓርላማ ዲፕሎማሲ ተግባራትን ትኩረት በመስጠት ማከናወኑን አብራርተዋል። ምክር ቤቱ ባሉት 13 ቋሚ ኮሚቴዎች በአስፈፃሚ አካላት እቅድ ላይ ክትትልና ድጋፍ ማድረጉንም በሪፖርቱ አንስተዋል። የምክር ቤቱ አባላት በዓመት ሁለት ጊዜ የሚያካሂዷቸው የምርጫ ክልል የውክልና ሥራም በአግባቡ እየተመራና ሕዝቡ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።   ሕጎች ከመፅደቃቸው በፊትም በየደረጃው ያሉ የምክር ቤቱ የሕግ ክፍል ባለሙያዎችና የቋሚ ኮሚቴ አባላት ዝርዝር ምርመራ እንደሚያደርጉበት አስታውቀዋል። ከዚህ ባለፈ የአስረጂና የሕዝብ ውይይት መድረኮችን በማመቻቸት በህጎቹ ላይ ግልፅነት እንዲፈጠር ተደርጓል ነው ያሉት። በበጀት ዓመቱ ምክር ቤቱ ባካሄዳቸው 43 መደበኛ እና ልዩ ስብሰባዎች ከ50 በላይ አዋጆችን መርምሮ ማፅደቁን ነው የገለፁት። ምክር ቤቱ በ2017 በጀት ዓመት ለሀገርና ሕዝብ ሁለንተናዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ሕጎች መርምሮ ማፅደቁን አብራርተዋል። የምክር ቤቱ አባላት በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ የተልዕኮ ስራዎች የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገባቸውን ገልጸዋል። ይሁንና ከውክልና ስራ ጋር ተያይዞ ህዝቡ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች ላይ አስፈጻሚ አካላት የእርምት እርምጃ ከመውሰድ ጋር ተያይዞ የሚታዩ ክፍተቶች በቀጣይ ዓመት በትኩረት ሊሰራባቸው ይገባል ብለዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ምክር ቤቱ የሚያወጣቸው ሕጎች በአግባቡ መፈፀማቸውን ኦዲት ማድረግ መጀመሩን አስታውቀዋል። የምክር ቤቱ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎችም በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሰረት እየተመሩና የተጠያቂነት አሰራርም ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ምክር ቤቱ ሕግ የማውጣት፣ የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የውክልና ሥራን ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት እንዲከናወን የማድረግ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ምክር ቤቱ በበጀት ዓመቱ በእቅድ የያዛቸውን ተግባራት ለማሳካት ያደረገው ርብርብ ውጤታማ እንደነበር ነው የገለጹት። በቀጣዩ በምክር ቤቱ አምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመን የነበሩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል ያጋጠሙ ክፍተቶችን በመሙላት የተሻለ ሥራ ለመከወን ሁሉም አባላት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ኢትዮጵያ በጉባኤው ላይ ብሄራዊ ጥቅሟንና የገለልተኝነት መርህን አማክላ አቋሟን በሚገባ አንጸባርቃለች- ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር)
Jul 7, 2025 169
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በ17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ብሄራዊ ጥቅሟንና የገለልተኝነት መርህን ማዕከል አድርጋ አቋሟን በሚገባ ማንጸባረቋን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። 17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ ተካሄዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው በጉባኤው ላይ ተሳትፈዋል። ሚኒስትሩ ጉባኤውን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ ሪዮ ዴጄኔሮ ያቀኑት በጉባኤው ላይ ለመሳተፍና ከሀገራት መሪዎች ጋር በመወያያት የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከርን ዓላማ በማድረግ መሆኑን ገልጸዋል። መሪዎቹ ከተወያዩባቸው አበይት አጀንዳዎች መካከል አካታች እና ፍትሃዊ የዓለም አስተዳደር ስርዓት እና ሪፎርም ይገኝበታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም እና የገለልተኝነት መርህን መሰረት በማድረግ ዓለም ሁሉንም አካባቢ ማቀፍ እንደሚገባው እና የአፍሪካ ድምጽ በሁሉም የዓለም ተቋማት እኩል መደመጥ እንዳለበት ማንሳታቸውን ነው ሚኒስትሩ የገለጹት። አፍሪካ ከመደመጥ ባሻገር ተሳትፎዋ ሊያድግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው መናገራቸውን አመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የደቡብ ለደቡብ ትብብርን ማጠናከርን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት የረጅም ጊዜ ስልጣኔ፣ ብዝሃ ባህል እና ታሪክ ያላት ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላትን የባህልና የኢኮኖሚ ትብብር ለማጠናከር እና ልምድ ለመቅሰም እንደምትሰራ ተናግረዋል። ከኢኮኖሚ እና ከፋይናንስ ጋር በተገናኘም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከብሪክስ ጋር ባላት ትብብር ተጠቃሚ እየሆነች እንደምትገኝ ገልጸዋል። የብሪክስ ልማት ባንክ አይነት የፋይናንስ ተቋም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ኢ-ፍትሃዊ የፋይናንስ እና የብድር አቅርቦት አማራጭ መሆናቸውንና ኢትዮጵያ ከዚህ ተጠቃሚ እንደምትሆን ነው ያነሱት። ዲጂታላዜሽን እና ሰው ሰራሽ አስተውሎትም ሌላኛው የውይይት ርዕሰ ጉዳይ ነበር። ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ዓለሙ ይዞ የመጣቸውን መልካም እድሎች የበለጠ መጠቀም እና ስጋቶችን ለመቀነስ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ መናገራቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ሰፋፊ ስራዎችን እያከናወነች እንደምትገኝ እና በዘርፉ ከብሪክስ ሀገራት ጋር በትብብር መስራት እንደምትሻ ጠቅሰዋል። ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከንግግር ባለፈ በተግባር ለዓለም ምሳሌ የሚሆን ስራ እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል። ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በአጠቃላይ በብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ የተሳካ ተሳትፎ ማድረጓን ጠቁመዋል።
ማህበራዊ
በክልሉ ከ8 ሺህ በላይ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እና ጥገና ይከናወናል
Jul 8, 2025 79
ባህርዳር፤ ሐምሌ 1/2017 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ8 ሺህ በላይ የአቅመ ደካማ ቤቶችን የመገንባት እና የመጠገን ስራ እንደሚከናወን ተገለጸ። ክልላዊ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ በባህርዳር ከተማ ጣና ክፍለ ከተማ ዛሬ ተጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እንደገለጹት፤ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን እሴት መሰረት በማድረግ እየተከናወነ ይገኛል።   በጎ ፈቃደኞችም በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ፣ የአቅመ ደካሞችን መኖሪያ ቤት በመስራትና በመጠገን፣ የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት፣ የሰብል ልማትና ሌሎች ተግባራት ለማከናወን እንደተዘጋጁ አስታውቀዋል። በዚህም በክልል ደረጃ ከ8 ሺህ በላይ የአቅመ ደካሞችን መኖሪያ ቤት ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ በመገንባትና በመጠገን የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ ይደረጋል ብለዋል። ለዚህም የህዝብን አቅም ፣ የመንግስት እና የልማት ድርጅቶች ተሳትፎ በማጎልበት ተፈጻሚ እንደሚሆን ተናግረዋል። በሁሉም የክልሉ ዞኖች፣ የከተማ አተዳደሮችና ወረዳዎች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ዛሬ በይፋ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል። የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ የዳበረ ባህላዊ እሴታችን የሆነውን በጎነትን በመተግበር የብልፅግና ጉዞን እናረጋግጣለን ብለዋል።   የተጀመሩ ሰው ተኮር ስራዎችን በበጎ ፈቃድ ስራ በማጠናከር ወገኖችን መደገፍ ይገባናል ሲሉ አመልክተዋል። በከተማ አስተዳደሩ ባለፈው ዓመት የክረምት ወራት 375 የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶችን በመገንባትና በማደስ ለተጠቃሚዎች ማስረከብ መቻሉን አውስተዋል። በዘንድሮው ክረምትም ካለፈው ዓመት በተሻለ መልኩ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶችን ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ ገንብቶ ለማስረከብ በቂ ዝግጅት መደረጉንም አስታውቀዋል።   በክረምት በጎ ፈቃድ ክልላዊ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የሰሜን ጎጃም ዞንና የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።  
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አብሮነትን እና ትስስርን ለማጠናከር ጉልህ ሚና አለው- በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች
Jul 8, 2025 56
ወላይታ ሶዶ ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ባህሎችና ዕሴቶችን በማወቅ አብሮነትና ትስስርን ለማጠናከር እንደሚያስችል የአገልግሎቱ ተሳታፊ ወጣቶች ተናገሩ። የ4ኛው ዙር ወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በዛሬው ዕለት ወላይታ ሶዶ ከተማ የገቡ ሲሆን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደዋል።   በወቅቱም ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች፤ በየአካባቢው የሚደረግላቸው አቀባበል የህብረተሰቡን የቆየ አብሮነት እሴት እንደሚያሳይና ይህም የእርስ በርስ ትስስርን ለማጠናከር እንዳስቻለ መገንዘባቸውን ተናግረዋል። ከወጣቶቹ መካከል ወጣት ሐና ተስፋዬ ተግባሩ የሁሉም ክልል ወጣቶች ትስስራቸውን እንዲያጠናክሩ የሚያግዝ እንዲሁም ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን የሚያጎለብት መሆኑን ተናግራለች። በመሆኑም አብሮነትን በማጠናከር ነገ የምንረከባትን ሀገር ዛሬ እየሰራን እንገኛለን ብላለች።   ''ችግኝ በመትከል ለቀጣዩ ትውልድ የለመለመች ሀገርን ለማስረከብ የጀመርነውን ስራ ዘላቂ እንዲሆን እየሰራን ነው'' ያለው ወጣት ዮናስ ድማማው በበኩሉ በየተጓዙበት ሁሉ የህዝቡን ባህልና ወግ የማወቅ ዕድል ማግኘታቸውን ገልጿል። በጎነት ለበርካታ ወገኖች መድረስ የሚያስችል ከመሆኑም ባሻገር በህዝቡ ዘንድ ትስስርን የሚፈጥር በመሆኑ የሚጠበቅበትን ለመወጣት መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ማርቆስ ማቴዎስ የወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ወጣቶች ሀገራቸውን አውቀው ሌሎችንም እንዲያሳውቁ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። ዛሬ በወላይታ ሶዶ ከተማ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ማካሄዳቸውን ጠቁመው በክልሉ በሚኖራቸው ቆይታ የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን እንደሚያከናውኑም አስረድተዋል።   ከተጀመረ አራት ዓመት የሆነው የወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎት በወጣቶች መካከል ትስስር በመፍጠር ለሀገራዊ መግባባት አስተዋጽኦ ማበርከቱን የገለፁት ደግሞ በሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ እንደገና ፈቃዱ ናቸው። የጉዞው ዋና ዓላማም ወጣቶች በጎነትን ተለማምደው በወሰን ሳይገደቡ ለወገኖቻቸው እንዲደርሱ ማስቻል ነው ብለዋል። ዘንድሮ ከ12 ክልሎች እና 2 ከተማ መስተዳድሮች በአጠቃላይ 112 ወጣቶች መሳተፋቸውን ጠቁመው በየዓመቱ እያደገ በመጣው በዚህ ስራ አብሮነትን የሚያጠናክሩ በርካታ ተግባራት እንደሚከናወኑም ተናግረዋል።
የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በህብረት የመስራት እሴትን እያጠናከረ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ
Jul 8, 2025 65
ሠመራ፣ሐምሌ 1፣2017 (ኢዜአ) በአፋር ክልል እየተካሄደ ያለው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በህብረት የመስራት እሴትን ማጠናከሩን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን የአቅመ ደካማ ቤቶችን በማደስ አስጀምረዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይም ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት እየተካሄደ ያለው የክረምት ወቅት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በህብረት የመስራት እሴትን እያጠናከረ ነው።   ይህን በመጠቀም በዚህ ዓመት 170 ለሚሆኑ አቅመ ደካማ ወገኖች ቤት የማደስ ስራ እንደሚከናወን ገልፀው በሎጊያ ክፍለ ከተማ አራት ቤቶችን በማደስ ስራውን አስጀምረናል ብለዋል። የህዝቡን የመተጋገዝ እና የመደጋገፍ ነባር እሴት በመጠቀም በክልሉ ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የወጣቶች ባህልና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሐሚድ ዱላ እንደ ሀገር በክረምት ወራት በ14 የተለያዩ የበጎ አድራጎት ዘርፎች ከ300 ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል።   በበጎ ፈቃድ ዘርፎቹም ወጣቶችን በንቃት በማሳተፍ ለሀገራቸው የበኩላቸውን ሚና የሚወጡበትን ተግባር ለማቀላጠፍ መሰራቱን አስረድተዋል። አቅመ ደካማ ወገኖችን መርዳት የማህበረሰቡን የመተባበርና የመደጋገፍ ባህል ማጠናከር መሆኑን የገለፁት ደግሞ የሠመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ ሙሳ ናቸው። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክልልና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።  
ተረጂነትን ማስቀረት የሀገር ክብር እና የሉዓላዊነት ጉዳይ ነው-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ
Jul 8, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈንና ተረጂነትን ማስቀረት የሀገር ክብርና የሉዓላዊነት ጉዳይ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን "90 ዓመታትን የተሻገረ የሰብዓዊ አገልግሎት አሻራ” በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል።   የማህበሩ የበላይ ጠባቂ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ማህበሩ በኢትዮጵያ ፈተናዎች የተወለደ የርህራሄና የበጎነት መገለጫ ነው ብለዋል። የማህበሩ በጎ ተግባርም ከኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የሰብዓዊነት ተግባር ጋር የተቆራኘ መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ዓለምአቀፍ የሰብዓዊነት ስምምነቶችን ከመቀበሏ በፊትም ህብረተሰቡ ሰብዓዊነትን በተግባር የኖረ የደግነትና የርህራሄ እሴትን መገለጫው ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ መርህ አልባነትና ኢ-ሰብዓዊነት እየጎላ መምጣቱን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፥ የሰብዓዊ ድጋፎች መቀዛቀዝም ዋና መገለጫው መሆኑን አስገንዝበዋል። ይህን ታሳቢ በማድረግ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ቀጣይ ትኩረቱ የሰብዓዊ ተግባርን በራስ አቅም የማከናወን ዘላቂ አቅምን መገንባት ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።   በሀገር አቀፍ ደረጃ በምግብ ራስን ለመቻል፣ በኢኖቬሽን ራሳችንን ለማብቃት እንደምንተጋው ሁሉ ተረጂነትን ማስቀረትና ለተጎዱ ወገኖቻችን በራስ አቅም ሰብዓዊ ድጋፍ ማድረግ የክብር እና ሉዓላዊነት ጉዳይ አድርገን መስራት አለብን ብለዋል። በቀጣይ ማህበሩ 100 ዓመቱን ሲያከብር፣ ህዝባዊ መሰረቱን አስፍቶ፣ በእሳቤ ጥራት፣ በገንዘብና በእውቀት ራሱን ችሎ፣ ዘመኑን የዋጀ ህጋዊ ማዕቀፍ አበጅቶ፣ ከኢትዮጵያ አልፎ በቀጣናውና በአፍሪካ የሰብዓዊነት ተምሳሌት የሆነ ታላቅ ተቋም ሆኖ ሊገኝ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። ማህበሩ ባለፉት 90 ዓመታት ኢትዮጵያ ችግር ላይ በነበረችበት ወቅት ሁሉ ላከናወናቸው ሰብዓዊና የጀግንነት ተግባራት በኢትዮጵያ መንግስት ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የማህበሩ ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በመላ ሀገሪቱ መዋቅሩን በማስፋት የሰብዓዊ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልፀዋል።   ማህበሩ ዓላማውን ለማሳካት የሚያስችለውን አቅም እየፈጠረ መሆኑን ጠቅሰው፥ ለዚህ ደግሞ የመንግስት ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ነው ያነሱት። ማህበሩ በሚቀጥሉት አስር ዓመታት የአባላቱን ቁጥር 20 ሚሊየን በማድረስ ወጪውን በራስ አቅም የመሸፈን እቅድ መያዙንም አመልክተዋል። የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ እንዲሁም ከማህበሩ ጋር የሚሰሩ አጋር ድርጅቶች የማህበሩን ያልተቋረጠና እያደገ የመጣ ሰብዓዊ ድጋፍን አድንቀዋል። በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል በተከናወነው የበዓሉ ማጠቃለያ መርሃ-ግብር ማህበሩን ሲደግፉ የነበሩ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ተቋማት እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
ኢኮኖሚ
በአማራ ክልል ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት ይጠናከራሉ
Jul 8, 2025 66
ባሕርዳር ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የታክስ አስተዳደሩን በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓት በማዘመንና በማቀላጠፍ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚጠናከሩ ተገለጸ። የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ከሐምሌ ጀምሮ በየዓመቱ የሚካሄደውን የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች የንቅናቄ መድረክ ማምሻውን በባሕር ዳር ከተማ አካሄዷል።   በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ባደረጉት ንግግር፤ የክልሉን ልማት ለማፋጠን፣ ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈንና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም የታክስ አስተዳደሩን በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓት በማዘመን ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። ይህም አሰራሩን ቀልጣፋና ፍትሃዊ ማድረግ፣ የግብር ስወራን በመቆጣጠር፣ ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ግብር መረቡ ማስገባት ላይ የአዲሱ በጀት ዓመት ትኩረት መሆኑን ጠቅሰዋል። ለስኬታማነቱም በየደረጃው ያለው አመራር፣ የዘርፉ ባለሙያና ሌላው ባለድርሻ አካል በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ክብረት ማህሙድ በበኩላቸው፤ የክልሉ ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ ለልማት በማዋል በኩል ቀደም ሲል አበረታች ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል፡፡ በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከተለያዩ የገቢ አርዕስቶች 58 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ በክልሉ ለሚካሄዱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ማዋል መቻሉን ገልጸዋል። በተጀመረው አዲሱ የበጀት ዓመት በክልሉ የወጪ ፍላጎትን በራስ አቅም ለመሸፈን በገቢ አሰባሰቡ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ለዚህም አመራርና ባለሙያ እንዲሁም ግብር ግብር ከፋይ የሚጠበቅበትን በመክፈል ሁሉም ኃላፊነቱን በተገቢው ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በንቅናቄ መድረኩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬን ጨምሮ ሌሎች የስራ ሃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ግብርን በአግባቡ በመክፈል ለሀገር ልማትና እድገት የምናደርገውን አስተዋጽኦ እናጠናክራለን- የንግዱ ማህበረሰብ አባላት
Jul 8, 2025 68
ሐረር ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ግብርን በአግባቡ በመክፈል ለሀገር ልማትና እድገት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩ በሐረሪ ክልል የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተናገሩ። በሐረሪ ክልል ለታማኝና ከፍተኛ ግብር ከፋዮች እውቅና የመስጠት ስነ-ስርዓት ዛሬ ተካሄዷል።   በወቅቱም ታማኝና ከፍተኛ ግብር ከፋዮቹ እንደገለፁት፤ ግብርን በወቅቱና በአግባቡ በመክፈል ለሀገር ልማትና እድገት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ አጠናክረው ይቀጥላሉ።   በከተማው በዓይን ህክምና እና በሌሎች ኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩት ዶክተር ኑረዲን አብዲ እንዳሉት ህዝቡ ለሚያነሳው የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በግብር የሚሰበሰብ ገቢ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ግብር መክፈል “የውዴታ ግዴታ ነው” ያሉት ዶክተር ኑረዲን የተሻለች አገርን ለመገንባትና ለትውልድ ለማስተላለፍ ግብርን በወቅቱ መክፈል እንደሚገባና ለተሰጣቸውም እውቅና ምስጋና አቅርበዋል። ''ግብር የምንከፍለው ልማቱ ተሳልጦ የማህበረሰቡ ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ወሳኝ በመሆኑ ነው'' ያሉት ደግሞ በከተማው በሆቴል ስራ የተሰማሩት አቶ ወንድሙ ፈይሳ ናቸው።   ግብር በመክፈሌ የዜግነት ግዴታዬን ተወጥቻለሁ፤ በዚህም ሽልማት ተበርክቶልኛል፤ ሁሉም የሚጠበቅበትን ግብር በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታውን ሊወጣ ይገባል ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል። በከተማው በህክምና ሙያ ዘርፍ ላይ የተሰማሩት ዶክተር ኑረዲን አህመድ በበኩላቸው ግብርን በወቅቱ መክፈል የዜግነት ግዴታን ከመወጣት ባሻገር ለዜጎች የስራ እድልን ለመፍጠር ሚናው የጎላ በመሆኑ ሁሉም ሃላፊነቱን መወጣት አለበት ብለዋል።   በተያዘው በጀት ዓመት ከ4 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የክልሉን 63 በመቶ የልማት ወጪ የመሸፈን ስራ ለማከናወን ዕቅድ መያዙን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ያሲን አብዱላሂ ናቸው። በተለይ በክልሉ ግብርን በአግባቡ ለሚከፍሉ ታማኝ ግብር ከፋዮችም ምስጋና አቅርበዋል።     የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በክልሉ ግብር ከፋዩ ግብሩን በአግባቡ በመክፈል ግዴታውን እንዲወጣ አሳስበው ከታክስ ማጭበርበርና ግብር ስወራ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮችን በህግ አግባብ የመቅረፉ ተግባር ይጠናከራል ብለዋል።
የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ፕሮጀክት ነው
Jul 8, 2025 64
ሚዛን አማን፤ ሐምሌ 1/2017 (ኢዜአ)፡- የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ መገንባት የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ትልቅ ፕሮጀክት ነው ሲሉ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። የአውሮፕላን ማረፊያው የግንባታ ሥራ ያለበትን ደረጃ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በስፍራው በመገኘት ተመልክተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦለት እየተገነባ ያለው የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ የመንገዱ ሥራው ከ1 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር በላይ አስፋልት ለብሷል።   በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሚዛን አማን ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ፕሮጀክቱ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በተመለከቱበት ወቅት እንደገለጹት፤ የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ በሕዝብ ጥያቄ መነሻ እየተገነባ ያለ ትልቅ ፕሮጀክት ነው። የአካባቢውን የቱሪዝም አቅም ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር ዘላቂ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።   ቡና እና ቅመማ ቅመምን ጨምሮ ሌሎችም ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የግብርና ምርቶችን የግብይት ሂደት ለማሳለጥ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነም ጠቅሰዋል።የግንባታ ሂደቱ ጥሩ ደረጃ ላይ መሆኑን መረዳታቸውን ገልጸዋል። በምልከታው የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሸ ዋጌሾ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል ፣ የክልል እና የዞን የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።  
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ የምታቀርበው የአረንጓዴ ኃይል አማራጭ የአየር ንብረት ተጽዕኖን ለመከላከል ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያመላክት ነው
Jul 8, 2025 71
  አዲስ አበባ፤ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ሀገራት እያቀረበች ያለው አረንጓዴ የኃይል አማራጭ የአየር ንብረት ተጽእኖን ለመከላከል እና ከባቢ አየርን ለመጠበቅ ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ። 17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ ተካሄዷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ በጉባኤው ላይ ተሳትፏል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ልዑኩ በጉባኤው ላይ የነበረውን ተሳትፎ አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሚኒስትሯ በማብራሪያቸው ካነሷቸው ጉዳዮች መካከል፥ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል እየተጠቀመቻቸው ያሉ የታዳሽ ኃይል አማራጮች ይገኝበታል። ዓለም ላይ የአየር ንብረት ለውጥን አስመልክቶ በሚደረጉ ጉዳዮች ጎልተው ከሚሰሙ አጀንዳዎች መካከል ከብክለት ነጻ የኢነርጂ አጠቃቀም አንዱ እንደሆነ ገልጸዋል። ብዙ ሀገራት አብዛኛው የኃይል ምንጫቸው ከበካይ ምንጮች መሆናቸውን ጠቅሰው፥ ይህም በአየር ንብረት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እያሳደረ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ አብዛኛውን የኤሌክትሪክ ኃይል የምታገኘው ከታዳሽ የኃይል ምንጮች እንደሆነ ተናግረዋል። በተጨማሪም የፀሐይ፣የነፋስ እና ሌሎች የኢነርጂ አማራጮችን እየተጠቀመች እንደምትገኝም ነው ያነሱት። በተለይም የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከብክለት ነጻ የኃይል ምንጭ እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሯ፥ ለሀገሪቷ ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል። ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ምስራቅ አፍሪካ እና አጠቃላይ ለአፍሪካ ብርሃንን የሚሰጥ የኢነርጂ ምንጭ ነው ብለዋል። ግድቡ እያመነጨ የሚገኘው ኃይል ዓለም የሚፈልገውን ከበካይ ምንጭ ነጻ የሆነ ኢነርጂ መሆኑን የበለጠ ተቀባይነቱን እንደሚያሳድገው ተናግረዋል። በጥቅሉ ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ከብክለት ነጻ የሆነ ኢነርጂ በማቅረብ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በተግባር ማረጋገጧን አመልክተዋል። አረንጓዴ ኢነርጂ የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ምላሽ አካል መሆኑን ነው ሚኒስትሯ የገለጹት። ኢትዮጵያ በቀጣዩ ዓመት በብራዚል በሚካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ 30) እና በሌሎች የአየር ንብረት ለውጥ መድረኮች በታዳሽ ኃይል ልማት እያከናወነች ያለችውን ስራ በስፋት እንደምታስተዋውቅ ተናግረዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራን ማስፋት አለብን - የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ
Jul 8, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአህጉሪቷ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋት ሀገራት በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ፥ የስራ አጥነት ችግር የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአህጉሪቱ ፈተና መሆኑን አንስተዋል። የስራ አጥነት ችግርን ለማቃለል የአፍሪካ አገራት በጋራ በመስራት ከፍተኛ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ አንስተዋል። ስለሆነም አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የስራ ፈጠራን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር ላይ ትኩረት ተደርጎ መስራት እንደሚገባ አስታውቀዋል። ለዚህም ጥሬ ዕቃ መላክ ብቻ ሳይሆን ብዙ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ እሴት ጨማሪ የምርት ሰንሰለቶችን በመዘርጋት በዜጋ ተጠቃሚነትና በወጪ ንግድ ዕድገት ላይ ትኩረት ማድረግ የግድ ነው ብለዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ የፋይናንስ አካታችነት ስራዎችን በማሻሻልና የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣናን በመተግበር ተጨማሪ የሥራ ዕድሎችን መፍጠር አስፈላጊ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል። ዜጎች ለህገወጥ ስደት እንዳይዳረጉ፣ በሀገራቸው ሰርተው እንዲለወጡና ተከብረው እንዲኖሩ አህጉራዊ ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በስራ ገበያ መረጃ ስርዓት፣ በክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ እና በህጋዊ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝም አንስተዋል። በፎረሙ የፋይናንስ አካታችነት፣ የዲጂታልና የንግድ መሰረተ ልማቶች፣ የህግ ማዕቀፍ ክፍተቶች፣ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣና ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ጠቁመዋል።  
ኢትዮጵያ በሥራ ዕድል ፈጠራ ከአፍሪካ ሀገራትና ከአህጉራዊ ተቋማት ጋር ትብብሯን አጠናክራ ትቀጥላለች
Jul 8, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በክህሎት ልማት ዘርፍ ከአፍሪካ ሀገራትና ከአህጉራዊ ተቋማት ጋር ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል። ከፎረሙ በተጓዳኝ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ግሩፕ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።       የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚህ ወቅት እንደገለጹት ኢትዮጵያ ለወጣቶች የክህሎት ልማት እና የሥራ ዕድል ፈጠራ አበክራ እየሰራች ትገኛለች። በአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራን ተቋማዊ አድርጎ ከመተግበርና አሰራርን ከማመቻቸት አንጻር የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያም በክህሎት ልማት፣ በሥራ ገበያና መሰል ጉዳዮች ከአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ጋር ባለፉት ሶስት ዓመታት በጋራ ስትሰራ ቆይታለች ነው ያሉት።   በዛሬው እለት የተደረገው የመግባቢያ ስምምነትም ከድርጅቱ ጋር የሚሰሩ ስራዎችን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እና አህጉራዊ ትብብርን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ድርጅቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ቀጣናዊ ጽህፈት ቤት መክፈቱን ገልጸው፤ ይህም ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትስስር በማሳደግ በኩል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። የአፍሪካ ኤሌክትሮኒክ ትሬድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉዓለም ስዩም በበኩላቸው ተቋሙ በአፍሪካ ቀጣይነት ያለው የስራ እድል ፈጠራን ለማጎልበት እየሰራ ነው ብለዋል።   ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር የተደረገው ስምምነት በኢትዮጵያ የስራ እድል ፈጠራን ዘላቂነት ባለው መልኩ ለማስፋፋት የሚከናወኑ ስራዎች ላይ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል። በፋይናንስ ዘርፍና የገበያ ትስስር መፍጠር ስራዎች ላይ የተቀናጀ ድጋፍ በማድረግ የንግድ ድርጅቶችን አቅምና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ድጋፍ እንደሚያደርግም አብራርተዋል።
የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ ፈጠራ የተሞላበት የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መጠቀም ይገባል -የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ
Jul 8, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ ፈጠራ የተሞላበት የቴክኖሎጂ ውጤቶች መጠቀም እንደሚገባ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ። ቱሪዝም ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በሀገራችን የሚገኙ መዳረሻዎችን እና የቱሪዝም አገልግሎቶችን በተሻለ ሁኔታ በማስተዋወቅ “ቪዚት ኢትዮጵያ" የተሰኘ ሀገር በቀል የግብይት ድረገፅ በይፋ ስራ ጀምሯል። ቪዚት ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዕምቅ ሀብት፣ የቱሪዝም መዳረሻዎች ለአለም የሚያስተዋውቅ ድረገፅ መሆኑ ተገልጿል።   በይፋ ማድረጊያ መርሃግብሩ ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሀሚድ፣ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የቪዚት ኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻዎችንና አገልግሎት ሰጪዎችን የሚያስተዋውቅ እንዲሁም ቻት ቦትን ያካተተ ነው ተብሏል።   በዚህ ወቅት የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እንዳሉት ኢትዮጵያ በርካታ የቱሪዝም ፀጋዎች አሏት። የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ ፈጠራ የተሞላበት የቴክኖሎጂ ውጤቶች መጠቀም ይገባል ብለዋል። ቪዚት ኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻዎችን የተመለከተ ወቅታዊና ጥራቱን የጠበቀ መረጃ ማቅረብ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል። የቱሪዝም ዘርፍ ተዋንያንን በአንድ በይነ መረብ የሚያስተሳስር ነው ብለዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሀሚድ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የበለፀገ የባህል ስብጥርና የቱሪዝም ሀብት ያላት አገር መሆኗንም ገልጸዋል።   ያለንበት የዲጂታል ዘመን ጎብኚዎች ባሉበት በመሆን ቪዚት ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፉን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉበት ነው ብለዋል። ቪዚት ኢትዮጵያ ደህንነቱ የተጠበቀና ተጠቃሚን ማዕከል ያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል የፈጠሩ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን እየተገበረች ነው
Jul 8, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም አካባቢ እያከናወነቻቸው ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል እየፈጠሩ መሆኑን መገንዘባቸውን የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ተሳታፊዎች ገለጹ። በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው ሦስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም በአህጉሪቱ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም ለአፍሪካውያን ወጣቶች የሥራ እድል ለመፍጠር ትብብርን የሚያጎለብት እንደሆነ ተሳታፊዎች ገልጸዋል። ኡጋንዳዊው ተሳታፊ ናምጎ ጆብ እንደገለጸው፤ ፎረሙ በአፍሪካ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም በሥራ እድል ፈጠራ የተያዙ እቅዶችን በትብብር መተግበር ለአህጉሪቷ ወጣቶች ተስፋ የሚሰጥ ነው። ይህም አፍሪካውያን ወጣቶች በአገራቸው ሰርተው የመበልጸግ ርዕያቸውን እውን በማድረግ ከስደት እንደሚታደጋቸው ገልጿል። ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አዲስ አበባ የመጣው እ.ኤ.አ በ2023 እንደነበር በማስታወስ፤ አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ሲመጣ የአዲስ አበባ የመሰረተ ልማት መስፋፋትና የከተማዋ እድገት እንዳስገረመውም ጠቅሷል። የአዲስ አበባ ዘመናዊ መሰረተ ልማት፣ የከተማ ውበት፣ የጎዳናዎች ስፋትና ጽዳት "በአፍሪካ የአውሮፓ ከተማ ውስጥ እንዳለሁ ተሰምቶኛል" ሲል የከተማዋን ዕድገት አድንቋል። በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል የሚፈጥሩ መሆኑን መገንዘቡን በማንሳት፥ ኢትዮጵያ በብሩህ ተስፋ ጉዞ ላይ ናት ብለዋል። በኮሜሳ የሴት ነጋዴዎች ማህበር ፌዴሬሽን የቦርድ ሊቀ መንበር ሞሪን ሶቦይ ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡበት ወቅት የሚያገኙት አዳዲስ ለውጥ ሀገሪቱ በፈጣን እድገት ላይ መሆኗን የሚያመላክት እንደሆነ ገልጸዋል።   ሌሎች የአፍሪካ አገራትም ከኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ልምድ ሊወስዱ እንደሚገባ ጠቁመዋል። አዲስ አበባ በከተማ ውበት፣ እድገትና ጽዱ አካባቢን በመፍጠር እያሳየች ያለው ለውጥም ለመኖሪያ ምቹ ያደርጋታል ነው ያሉት። በኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ የስራ ድርጅት ዋና የቴክኒክ አማካሪ አንቶኒ አይንታ ኢትዮጵያ ለራሷ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት አገሮችም አቅም መሆን የሚችል ብቁ የሰው ሃይል አላት ብለዋል።   አህጉሪቱን በንግድና አገልግሎት ለማስተሳሰር ከተያዘው ራዕይ ጎን ለጎን በሰለጠነ የሰው ሃይል የወጣቶችን እውቀት በመጠቀም በስራ ፈጠራ ማስተሳሰር እንደሚቻል ጨምረዋል። ሦስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም የግብርና እሴት ሰንሰለት፣ ዲጂታላይዜሽንና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ አስተማማኝ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር ላይ ምክክር በማድረግ ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል።
ስፖርት
ቼልሲ ለፍጻሜ አለፈ
Jul 9, 2025 38
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ቼልሲ ፍሉሜኔንሴን 2 ለ 0 አሸንፏል። በሜትላይፍ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በ የ60 ሚሊዮን ፓውንድ ፈራሚው ጆአኦ ፔድሮ በ18ኛው እና 56ኛው ደቂቃ ላይ በግሩም ሁኔታ ያስቆጠራቸው ግቦች ቡድኑን አሸናፊ አድርጓል። ፔድሮ የልጅነት ክለቡ ላይ ግቦቹን ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን በተቀዛቀዘ መልኩ ገልጿል። ጨዋታው ተመጣጣኝ እና ጠንካራ ፉክክር ተደርጎበታል። ቼልሲ ለግብ የቀረቡ እድሎችን በመፍጠር የተሻለ ነበር። ጠንካራው የፍሉሜንሴ የተከላካይ መስመር በጨዋታው ላይ ባልተለመደ ሁኔታ ስህተቶችን ሲሰራ ተስተውሏል። ቡድኑ ከ11 ጨዋታዎች በኋላ ሽንፈት አስተናግዷል። የቼልሲ የአማካይ ተጫዋች ሞሰስ ካሲዬዶ በጉዳት ምክንያት በጨዋታው ማብቂያ ላይ ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። ዋንጫውን ለማንሳት ከፒኤስጂ እና ሪያል ማድሪድ አሸናፊ ጋር ያደርጋል። ፒኤስጂ እና ሪያል ማድሪድ ነገ የሚያደርጉት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
በመዲናዋ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ
Jul 8, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። በዛሬው ዕለት በ11 ክፍለ ከተሞች ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎባቸው የተገነቡ 122 የስፖርት ማዘውተሪያ እና 1ሺህ 155 የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዛሬ ማለዳ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ መሪ ሎቄ 40/60 ኮንዶሚኒየም አካባቢና በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት መጫወቻ መሰረተ ልማቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። ከንቲባዋ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ከተማ አስተዳደሩ በ2017 በጀት ዓመት 15ሺህ 960 ፕሮጀክቶች ገንብቶ አጠናቋል። መሰረተ ልማቶቹን ለመገንባት ከወጣው ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ 50 በመቶ የሚሆነው በከተማዋ ነዋሪዎች መሸፈኑን ነው የተናገሩት።   አስተዳደሩ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ3ሺህ 800 በላይ የህፃናት የመጫወቻ ስፍራዎችን መገንባቱንም ገልጸዋል። ጊዜን፣ እውቀትንና የማህበረሰቡን ተሳትፎ በማቀናጀት ለህፃናት እና ለወጣቶች ቅድሚያ በመስጠት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል። ስራዎቹ ህፃናትና ወጣቶች በአካልና በአዕምሮ ብቁ ሆነው እንዲያድጉ የሚያስችሉ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በቀጣይ በስፖርቱ ዘርፍ በዓለምና በአህጉር መድረክ የተሻለ ውጤት ለማምጣት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ በላይ ደጀን በበኩላቸው፤ በከተማዋ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በአዕምሮና በአካል የዳበረ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመገንባት ተቀሜታቸው የጎላ ነው ብለዋል።
ፍሉሜኔንሴ እና ቼልሲ ለክለቦች የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ለማለፍ ይፋለማሉ 
Jul 8, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ የግማሽ ፍጻሜ መርሃ ግብር ፍሉሜኔንሴ እና ቼልሲ ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሜትላይፍ ስታዲየም ይካሄዳል። የብራዚሉ ፍሉሜኔንሴ በሩብ ፍጻሜው የሳዕዲ አረቢያውን አል ሂላልን 2 ለ 1 አሸንፏል። የእንግሊዙ ቼልሲ የብራዚሉን ፓልሜራስ 2 ለ 1 በመርታት የመጨረሻ አራት ውስጥ ገብቷል። ባለፉት 11 ጨዋታዎችን ሽንፈትን ያላየው ፍሉሜኔንሴ በዓለም ዋንጫው ግምቶችን ፉርሽ በማድረግ ግማሽ ፍጻሜ ደርሷል። ጠንካራ የተከላካይ ክፍል መስመሩ እና የመልሶ ማጥቃት የአጨዋወት ስልቱ ለተጋጣሚው ራስ ምታት ሆኗል። በሬናቶ ጋውቼ የሚመራው ፍሉሚኔንሴ በባለፈው የውድድር ዓመት በብራዚል ሴሪ አ ከመውረድ ተርፎ በአጭር ጊዜ እያሳየ ያለው አስገራሚ ብቃት አሰልጣኙን አስወድሷቸዋል። የኢንዞ ማሬስካው ቼልሲ በፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ በአማካይ ተጫዋቹ የፈጠራ አቅም፣ የታክቲክ ተለዋዋጭነት እና የኳስ የመቆጣጠር አቅም ታግዞ ጥሩ ግስጋሴ እያደረገ ይገኛል። ይሁንና የተከላካይ ክፍል መስመሩ ተጋላጭነት ተጋጣሚዎቹ ግብ እንዲያስቆጥርበት ሲያደርጉ ለመመልከት ተችሏል። ሁለቱ ቡድኖች እርስ በእርስ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የእግር ኳስ ልሂቃኑ እና ተመልካቹ ለቼልሲ የማሸነፍ እድሉን በስፋት ቢሰጡም ተጋጣሚው ፍሉሜኔንሴ ያልተጠበቀ ድል ሊያስመዘግብበት እድል አለ የሚሉ አልጠፉም። ቼልሲ ጨዋታውን ለማሸነፍ ጠንካራውን የብራዚል ክለብ የመከላከል ግድግዳ ማፍረስ ይጠበቅበታል። ፍሉሜኔንሴ ጠንካራ የመከላከል ቅርጹን ጠብቆ በሚያገኛቸው አጋጣሚዎች በመልሶ ማጥቃት ግቦችን ለማስቆጠር የሚያስችል የጨዋታ ስልት ወደ ሜዳ ይዞ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። የፍሉሜንሴው ብራዚላዊ የ40 ዓመት አምበል ቲያጎ ሲልቫ የቀድሞ ክለቡን ቼልሲን የሚገጥምበት ጨዋታ መሆኑንም ትኩረት ስቧል። የ36 ዓመቱ ፈረተንሳዊ ፍራንስዊ ሌቲክሲየር ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ በፍጻሜው ከፒኤስጂ ወይም ከሪያል ማድሪድ አሸናፊ ጋር ይገናኛል። በአሜሪካ አስተጋጅነት እየተካሄደ ያለው የፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ ዛሬ 22ኛ ቀኑን ይዟል።
አካባቢ ጥበቃ
በክልሉ የፍራፍሬ እና የደን ችግኞችን በግል ማሳና የወል መሬት ላይ በማልማት ለዘላቂ ተጠቃሚነት መትጋት ይገባል
Jul 8, 2025 68
ባሕርዳር፤ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የፍራፍሬ ፣ የደን እና የእንስሳት መኖ ችግኞችን በግል ማሳና በወል መሬት ላይ በመትከልና በማልማት ለዘላቂ ተጠቃሚነት መትጋት እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ አሳሰቡ። "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በሰሜን ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ በአቦላ ተራራ ተፋሰስ ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ተጀምሯል።   የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በመርሃ ግብሩ ባደረጉት ንግግር፤ ችግሮችን የምንሻገረው የተራቆቱ አካባቢዎችን በችግኝ ተከላ አረንጓዴ በማልበስ ሁለንተናዊ ልማትን ማፋጠን ስንችል ነው ብለዋል። ችግኝ በመትከል የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቋቋም ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚቻል ህዝቡ ተገንዝቦ ለአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ሙሉ አቅሙን ተጠቅመን መስራት አለብን ሲሉ ገልጸዋል። የተተከለውን ተንከባክቦ ማሳደግ የሁሉም ኃላፊነት መሆን እንዳለበትም አመልክተዋል። በመርሃ ግብሩም የፍራፍሬ፣ የደንና የእንስሳት መኖ ችግኞችን በግል ማሳና በወል መሬት ላይ በመትከልና በማልማት ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መትጋት እንደሚገባ ገልጸዋል። በየደረጃው የሚገኘው አመራርና የዘርፉ ባለሙያም ሳይንሳዊ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን ለማስፈፀም ሊረባረቡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የግብርና ሚኒስቴር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና ሌሎች የግብርና ስራዎች እያደረገ ያለው ድጋፍ ያመሰገኑት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በቀጣይም እገዛውን አጠናክሮ እንዲቀጠልም አመልክተዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤልያስ በበኩላቸው፤ የደን ሀብትን ጠብቆ ይበልጥ ለማሳደግ የተጀመረው ችግኝ ተከላ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   ባለፉት ሰባት ዓመታት እንደሀገር በአረንጓዴ አሻራ የተተከለው ችግኝ የፅድቀት ምጣኔውም 80 በመቶ ማድረስ መቻሉን አረጋግጠዋል። ዛሬ በአማራ ክልል ይልማና ዴንሳ ወረዳ በአቦላ ተራራ ተፋሰስ የተተከለው ችግኝም የአካባቢው ሕብረተሰብ የቱሩፋቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ተንከባክቦ እንዲያሳድግ መልእክት አስተላልፈዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ክላስተር ዘርፍ አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር ) ፤ በክልሉ ሁሉም አካባቢ ዛሬ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በይፋ መጀመሩን አስታውቀዋል።   ለችግኝ ተከላውም 1 ነጥብ 55 ቢሊዮን ችግኝ መዘጋጀቱን ጠቅሰው፤ ከዚህም ውስጥ 20 ሚሊዮን የሚሆነው ቡናን ጨምሮ የተለያዩ ፍራፍሬዎች እንደሆኑ ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች የክልሉን መልካም ገፅታ ይበልጥ ከማጉላት ባሻገር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት በማሳደግ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል። ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል፣ የክልልና የዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።  
የአረንጓዴ አሻራ ልማት ለግብርና ምርትና ምርታማነት ማደግ ጉልህ ሚና እያበረከተ ነው
Jul 8, 2025 69
ወልቂጤ ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር ስራዎች ለግብርና ምርትና ምርታማነት ማደግ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) አመለከቱ። ርዕሰ መስተዳድሩ ዛሬ በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ አበኬ ቀበሌ ዌራ ንዑስ ተፋሰስ ላይ የ2017 ዓ.ም የክረምት ወቅት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን በይፋ አስጀምረዋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተከናወኑ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲያድግ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው። በዚህም የአፈር ለምነት መመለስና ማስጠበቅ እንዲሁም የደረቁ ምንጮች ማገገም መቻላቸውን አንስተው በተፈጥሮ ላይ የተሰራ ስራ በመሆኑ ሁሉን አቀፍ በሆነ መልኩ ውጤት እያስገኘ ነው ብለዋል። የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ ሳቢና ምቹ የመኖሪያ አካባቢዎች እንዲፈጠሩ ማድረጉን አመልክተዋል። የክልሉ ህብረተሰብም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርን ባህል እያደረገ መምጣቱን ጠቅሰው የተጀመረውን ተፈጥሮን የመንከባከብ ስራ አጠናክሮ ሊያስቀጥል እንደሚገባም አሳስበዋል።   በምክትል ርዕሰ መስተዳዳር ማእረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ስሩር በክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ ልማት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ላላቸው የፍራፍሬ፣ የመኖ፣ የደን እና የቡና ችግኞች ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።   በክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርም ከ1 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ገልፀው መትከል ብቻ ሳይሆን የተተከለው እንዲጸድቅ ተገቢ እንክብካቤ ሊደረግ ይገባል ብለዋል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ካቢኔ አባላትና የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።  
አገር የሚገነባው በተባበረ ሁለንተናዊ የህዝብ ተሳትፎ ነው -ሚኒስትር አህመድ ሽዴ
Jul 8, 2025 70
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦አገር የሚገነባው በተባበረ ሁለንተናዊ የህዝብ ተሳትፎ በመሆኑ ሁሉም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚጠበቅበት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ፡፡ የ2017 አገር-አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ መጀመሩ ይታወቃል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር፣የፕላንና ልማት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራር አባላትና ባለሙያዎች እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የስራ ኃላፊዎች በእንጦጦ ፓርክ ዛሬ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ አገር የሚገነባው በተባበረ ሁለንተናዊ የህዝብ ተሳትፎ መሆኑን ገልጸው፤ ለዚህም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተገኘው ውጤት ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሮች የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን ጠቁመው፥ይህም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ እውቅና እንድታገኝ ማድረጉን ተናግረዋል። በአረንጓዴ አሻራ ውጤት የተመዘገበው በከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎ መሆኑንም አስረድተዋል። አሁን ላይ በአገራችን ችግኝ ተክሎ መንከባከብ እና ማሳደግ የህብረተሰቡ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት መንግስት ስትራቴጂዎችን ነድፎ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አረንጓዴ አሻራ አንዱ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ በበኩላቸው፥የዛሬው የአረንጓዴ አሻራና የጽዱ ኢትዮጵያ መርሃ ግብር ዋና ዓላማ ጽዳትንና ውበትን ባህሉ ያደረገ ትውልድ ለመፍጠር ነው ብለዋል፡፡   በመላ አገሪቷ ጽዱ ኢትዮጵያን እውን የማድረግ የስድስት ወር ንቅናቄ በይፋ መጀመሩንም ተናግረዋል፡፡ በአረንጓዴ አሻራና በጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ መርሃ ግብሮች ህብረተሰቡን በማሳተፍ የውሃ፣የአየርና የአፈር ብክለትን ለመከላከል እንደሚሰራ ነው የገለጹት። የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ በበኩላቸው፤በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን ከመትከል ባሻገር የጽድቀት መጠናቸውን ለመጨመር የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራም አመልክተዋል፡፡   በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን መትከል የህብረተሰቡን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) ናቸው፡፡   ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በተጨማሪም የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመላክቷል፡፡
አረንጓዴ አሻራ ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር የምንገነባበት የጋራ የልማት ስራችን ነው
Jul 8, 2025 77
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር የምንገነባበት የጋራ የልማት ስራችን ነው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አመራሮችና ሰራተኞች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ( ዶ/ር) በየካ ተራራ በመገኘት ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አመራር አባላት እና ሰራተኞች ጋር የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።   የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩም ቀደም ብሎ ለአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በተዘጋጀ ስፍራ ላይ ተከናውኗል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የተሳተፉት የጽህፈት ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት እንደገለጹት ኢትዮጵያ በብዝሃ ዘርፍ እያከናወነች ባለው ተግባር ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል። የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አረንጓዴ አሻራ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ስለመሆኑም አንስተዋል። አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር የምንገነባበት የጋራ የልማት ስራችን ነው ሲሉም አስተያየት ሰጪዎቹ አክለዋል።   የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶች እና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር ቀጄላ መርዳሳ እንዳሉት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በዓለም አቀፍ ደረጃ ምሳሌ የሚያደርጋት ነው ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች እንዲተከሉ በማድረግ ለአረንጓዴ ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ተናግረዋል።   ተግባሩ ከሀገር ባለፈ ለአለም የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል አስተዋጽኦ ማበርከት መቻሉን በተግባር ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ቀንአ ያደታ (ዶ/ር) በበኩላቸው አረንጓዴ አሻራ የኢትዮጵያ የልማትና የብልጽግና ጉዞ አካል ነው ብለዋል። መርሃ-ግብሩ በርካታ አላማዎችን ያነገበ ሲሆን በተለይም የአካባቢ ጥበቃ፣የአየር ንብረት ለውጥና በምግብ ራስን የመቻል አንዱ ማሳያ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡   እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በጋራ የሚሰባሰቡበትና አብሮነታቸውን የሚያጠናክሩበት መሆኑ ደግሞ ለአገረ መንግስት ግንባታው ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ስለመሆኑም አንስተዋል። በዚህ ሒደት አረንጓዴ አሻራ ለመጪው ትውልድ ምቹና እድገቷ የተረጋገጠች አገርን ለማስረከብ አይነተኛ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮች እና የሴክተሮች ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ እንዳሉት ባለፉት የለውጥ አመታት አረንጓዴ አሻራ ተከታታይነት ባለው መልኩ ተግባራዊ መደረጉ እንደ አገር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታን አስገኝቷል።   መርሃ-ግብሩን በአግባቡ በማስቀጠል ረገድ ዜጎች እያደረጉት ያለው ርብርብ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለው አረንጓዴ አሻራ የተፈጥሮ ሃብትን በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋልና ምቹ በማድረግ ረገድ ከራሷ አልፎ አህጉሪቷን በልማት ማስተሳሰር የሚያስችል ስለመሆኑም አንስተዋል። አረንጓዴ አሻራ የቀጣዩ ትውልድ ጥቅምን ታሳቢ ያደረገና ለዘላቂ ልማት መረጋገጥ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ ዜጎች በጀመሩት ልክ ተግባሩን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሮጀክቶች አስተባባሪ ሚኒስትር ዴኤታ ብርሃኑ ተስፋዬ አረንጓዴ አሻራ በአገሪቱ የተጀመረውን ፈጣን የልማት እንቅስቃሴ ከግብ ለማድረስ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ገልጸዋል።   የተሻለች ኢትዮጵያን ለትውልዱ ለማስተላለፍ የሚደረገውን ጥረት ከዳር ለማድረስ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸው አረንጓዴ አሻራ አንዱ ማሳያ ስለመሆኑ አብራርተዋል። በመሆኑም በአረንጓዴ አሻራ የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል ሁሉም ዜጋ የቤት ስራው አድርጎ በሃላፊነት ሊሰራ እንደሚገባ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ደን ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳመነ ዳሮታ አረንጓዴ አሻራ በኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃና በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ የሚታይ ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል። እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነትን በመጨመር፣ የተፋሰስ ስራውን በማጠናከርና የተፈጥሮ ሃብትን ወደ ጥቅም በመቀየር ረገድ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።   የኢትዮጵያን ብልጽግና ከሚያሳኩ ተግባራት አንዱ አረንጓዴ አሻራ መሆኑን የገለጹት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ መርሃ-ግብሩ በሚፈለገው መልኩ ተግባራዊ ሆኖ እንዲቀጥል ተቋሙ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል።  
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 756
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ።   በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1230
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል።   የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 906
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል።   ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1532
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
የህንድ የፈጠራ ማዕከል - ባንጋሎሩ
Jul 2, 2025 294
ቤተልሄም ባህሩ(ኢዜአ) የዴልሂና አግራ ቆይታችንን ጨርሰን ወደ ቀጣይ መዳረሻችን ባንጋሎሩ ከተማ ልንጓዝ ስንሰናዳ አብዛኛው የጋዜጠኛ ልዑክ ያሳሰበው እንደሰም የምታቀልጠውን የአግራ ፀሀይና ሙቀት በባንጋሎሩም ታገኘን ይሆን? የሚለው ነበር። ሆኖም ከዴልሂ ኢንድራ ጋንዲ አየር ማረፊያ ተነስተን ለሶስት ሰዓት ከተቃረበ በረራ በኋላ ያገኘናት ባንጋሎሩ የተለየች ሆነን አገኘናት። ባንጋሎሩ ቀዝቀዝ ባለ አየር ነበር እንግዶቿን የተቀበለችን። በዕለቱ ከክፍሎቻችን ወጥተን በጋራ ወደአየር ማረፊያ የሚወስደንን ትራንስፖርት ስንጠባበቅ ከጋዜጠኛ ቡድኑ ስድስት አባላት ከአጠገባችን እንዳልነበሩ አስተዋልን። የት ጋር እንደተነጣጠልን አላስታውስም። በዚህ ምክንያት ግን የእለቱ ጉዟችን ተሰርዞ ከተማዋን ለማየት ስንዘዋወር የማውቀው ዓይነት እንጂ የተለየ ሙቀት አላስተናገድኩም። የ13 ወር ፀጋ በመባል የምትታወቀው አገሬ ኢትዮጵያ ከዳሎል እስከ ራስ ዳሽን ባላት የመልከዓ ምድር አቀማመጥና ልዩ ልዩ የአየር ጠባይ ሙቀቱንም፣ ቅዝቃዜውንም ማወቃችን እንደዚህ ለአለ አጋጣሚ መልካም ስሜት ይፈጥራል። በተወሰነ ደረጃ በህንድ ያጋጠመኝ የአየር ባህሪ ከአገሬ ጋር ቢመሳሰልብኝ የፈጣሪንና የተፈጥሮን ስራ አጃኢብ ብዬ እንዳልፍ አድርጎኛል። ባንጋሎሩ ከተማ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ማዕከል በመሆኗ የህንድ ሲልከን ቫሊ በመባል ትታወቃለች። ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ስፍራዎችም ከመገለጫዎቿ መካከል ናቸው። የጠፈር ጠበብቶቹ - ባንጋሎሩ ደርሰን በመጀመሪያ ያየነው ዓለም በስፔስ ሳይንስ እየሰራች ያለችውና እያስመዘገበችው የምትገኘው ውጤት ማሳያ የሆነውን የህንድ ስፔስ ምርምር ድርጅትን ነው። ተቋሙ የህንድ መንግስት የስፔስ ዲፓርትመንት አካል ሲሆን፤ ዶክተር ቪክራም ሳራብሃይ በተሰኙ ባለራዕይ በ1962 የተወጠነና አሁን ላይ በዘርፉ ተገዳዳሪ መሆን የቻለ ነው። የተቋሙ ዓላማ የስፔስ ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመተግበር ለተለያዩ አገራዊ ጥቅሞች ማዋል መሆኑን ተከትሎ የሳተላይት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማምረት ስራን ጨምሮ ከአገሩ አልፎ ለሌሎች አገራትም በዘርፉ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። የተደረገልን ገለፃ አብዛኛውን ጋዜጠኛ ያስደመመ ነበር ከገለፃ በኋላ በጋዜጠኞች የተነሳው ሃሳብም ህንድ በስፔስ ዘርፍ ያላት ልምድና ያከናወነችው ተግባር በቀጣይም ልትሰራ የወጠነቻቸው ሃሳቦች የአገሪቱን መዳረሻ የተለሙ በአገራቸው እንዲተገበር የሚናፍቁት መሆኑን ነው። ተቋሙ በዘርፉ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም ትብብሩን የሚያጠናክር መሆኑን ከተደረገልን ገለፃ ተገንዝበናል።   በሳይንስ፣ ኢንጂነሪንግና አስተዳደር ምሁራንን በማስተማር እያበረከተ ያለው የህንድ የሳይንስ ኢንስቲትዩት በባንጋሎሩ ከጎበኘናቸው መካከል የሚጠቀስ ነው። ኢንስቲትዩቱ ከአፍሪካ የተውጣጡ ተማሪዎችን የሚያስተምርና ከተቋማት ጋርም በዘርፉ የሚሰራ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ከጅማ፣ በተግባር ለመቀየር ሲታትሩ የስታርት አፖችን የምርት ውጤቶቻቸውን ሲፈትሹና ሲሞክሩ ተመልክቻለሁ። በኢትዮጵያም አሁን ላይ ለስታርት አፖች በተሰጠው ትኩረትና በተፈጠረው ምቹ ስነ ምህዳር የፈጠራ ውጤቶች እያደጉና እየተበራከቱ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። እንደ አዳማና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተቋማት የተማሪዎችን ፈጠራ ወደ ውጤት ለመቀየር እየተጉ መሆኑና የስታርት አፕ ኤግዚቢሽንና የሰመር ቡት ካምፖች ፈጠራን ምን ያህል እያበራከቱ መሆናቸው በጉብኝቱ ወቅት ወደ አዕምሮዬ የመጣ የአገሬው ህዝብ በውጤት የታጀበ ጥረት ነው።   ከአራት አስርት ዓመታት በላይ በባዩቴክኖሎጂ ዘርፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘው ባዮኮንም ከባላንጎሩ የጉብኝት መዳረሻችን መካከል የሆነና አስፈላጊ መድሀኒቶችን የሚያመርትና በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይም እየሰራ ያለ ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት የአቅም ግንባታ ስልጠናው ተጠቃሚ ናቸው። ከ120 በላይ በሆኑ አገራት ለስኳርና ካንሰር ህመም የሚያገለገሉ መድሀኒቶችን በማምረትና በማሰራጨት ለህሙማን ፈውስና ለጤናው ዘርፍ ስርዓት አስተዋፅኦ እያበረከተም ይገኛል። የተቋሙ ላቦራቶሪና ዘመኑን የዋጀና ደረጃውን የጠበቀ ማምረቻ ፋብሪካን መጎብኘቴ አለም በፋርማሲዩቲካልስ ዘርፍ ያለችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። የባንጋሎሩ ቤተመንግስት - ይህን ቤተ መንግስት ማስቃኘቴን ከመጀመሬ በፊት በስፍራው ካስገረመኝ ነገር ላወጋችሁ ወደድኩ። ቤተ መንግስቱን ለመጎብኘት ያቀናነው በእለተ ሰኞ ነበር። ሆኖም ምድረ ግቢውን ቃኝተን ስለህንፃው ሰምተን ከመመለስ ውጪ ወደ ውስጥ አልዘለቅንም። ለምን? ለሚለው ምላሹ በዚህ ስፍራ "ሰኞ የእረፍት ቀን ናት" ነው። እንዴት ካላችሁ ቤተ መንግስቱ ቅዳሜና እሁድ በበርካታ ሰዎች የሚጎበኝ መሆኑን ተከትሎ በስፍራው ለሚሰሩ ሰራተኞች የእረፍት ቀናቸው ሰኞ በመሆኑ ነው። የቤተ መንግስቱ ምድረ ግቢ ሰፊና ልምላሜ የተላበሰ ሲሆን፤ የሚያምርና ለዓይን የሚስብ ኪነ ህንፃ ያለው ነው። አሰራሩና ውጥኑም እንደሚከተለው ነው። በዎዲየር ስርወ መንግስት ንጉስ ቻማራጃ ዋዲያር ወደ እንግሊዝ ባደረጉት ጉዞ በለንደን ዊንሶር ግንብ ይደነቃል። ተደንቆም አልቀረ የባንጋሎሩ ቤተ መንግስትን በተመሳሳይ ሁኔታ ይገነባል። ይህ ቤተ መንግስት በተወሰነ መልኩ የመካከለኛው ዘመን የኖርማንሲና የእንግሊዝ ግንቦችን ይመስላል።   ቪድሃና ሶውዳ የካራንታካ ህግ አውጪ አካል መናገሻ በጉብኝታችን ያየነው ሌላው መዳረሻ ስፍራችን ነው። የህግ አውጪና የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የያዘው ይህ ህንፃ ህንድ ነፃነቷን ካገኘች በኋላ በራሷ መሀንዲስ የሰራችው የመጀመሪያው ህንፃ መሆኑ ተገልፆልናል። የህንፃ ግንባታ ጥበብ ማሳያ፣ የፖለቲካ መናገሻ እንዲሁም የባህል ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል።   እንደአጠቃላይ በቆይታዬ የተመለከትኩት የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ማበረታቻ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራ ኢትዮጵያ እያከናወነች ካለው የኮሪደር ልማትና ስታርት አፕን የማበረታታት ብሎም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ምቹነት ስራዎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ነው። በህንድና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ዘመናትን የተሻገረ፤ ለሁለት ሺህ ዓመታት የዘለቀ መሆኑን የታሪክ መዛግብት ያሳያል። የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት በአክሱም ስርወ መንግስት ኢትዮጵያና ህንድ በአዱሊስ ወደብ በኩል የንግድ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። በወቅቱ ኢትዮጵያ ቅመማ ቅመምና ሐርን ከህንድ ትገበይ ነበር። ህንድ ደግሞ ወርቅና የዝሆን ጥርስን ከኢትዮጵያ ትሸምት ነበር። ህንድ ከንግድ ልውውጥ ባሻገር በኢትዮጵያ ኪነ ህንፃ ግንባታ ላይ አሻራዋን አኑራለች። በኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍም ትልቅ አበርክቶ ያላት አገር ናት። ህንድ ነፃነቷን ካገኘችበት እኤአ 1948 አንስቶ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት ኢትዮጵያና ህንድ ሌላው የሚያመሳስላቸው ነገር ሆኖ ያገኘሁት የአምራች ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እያከናወኑ ያሉት ንቅናቄ ነው። ህንድ እ.አ.አ ከ2014 ጀምሮ የአምራች ዘርፉን ለማበረታታት "ሜድ ኢን ኢንዲያ" በሚል ለአስር ዓመት የተገበረችውና በርካታ ለውጥ የተመዘገበበት ንቅናቄ በኢትዮጵያ ከ2014ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ካለውና የሃገር በቀል ምርቶች እና አምራቾችን ማጠናከር፣ የኢንዱስትሪያል ማህበረሰብ ግንባታን ማሳደግ ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢ መፍጠር እና የጥናት እና ምርምር ችግር ፈቺነትን ማሳደግን ዓላማ ካደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ጋር የተመሳሰለ ነው። ንቅናቄ በኢትዮጵያ መተግበሩ ዓመታዊ የዘርፍ ዕድገት፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና ገቢ ምርት በመተካት በኩል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑም ይታወቃል። በህንድ ተዘዋውሬ በተመለከትካቸው ከተማዎች ባሉ ጎዳናዎች ከታዘብኩት ነገር ሰዎች ከሱቅ ለሚገበያዩት ነገር ሳይቀር በዲጂታል መንገድ ክፍያ መፈፀማቸውን ነው። በባጃጅና በሞተር የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘትም ጭምር ሞባይሉን በመጠቀም “ይህ ቦታ የት ነው?” ሳይል ያሻዎት ስፍራ መድረስም ሌላው ትዝብቴ ነው። ይህ ነገር በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትኩረት አግኝተው እየተሰራባቸው ካሉት የዲጂታል ክፍያና ዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ መርሃ ግብር ጋር የሚመሳሰል ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በቆይታችን ልክ እንደአትሌቶቻችን ሁሉ በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርጎ የሚያስነሳውን ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዝናና ክብር ለማስተዋል ችያለሁ። ፀጉረ ልውጥ መሆናችንን የተገነዘቡ በገበያ ማዕከላት የሚያገኙን እንዲሁም በምንጎበኛቸው ተቋማት የምንተዋወቃቸው ህንዳውያን "ከየት ናችሁ?" ብለው ሲጠይቁ፤ ለእኔና አንድ ከሌላ መገናኛ ብዙሃን የሄድን "ከኢትዮጵያዊ" ስንል የሚከተልልን ምላሽ "አሃ የኢትዮጵያ አየር መንገድ" የሚል ነው። ይህም አየር መንገዱ ስሙ ከኢትዮጵያ ተሰናስሎ የሚጠራ የአገሪቷ መታወቂያ ተቋም መሆኑን ያስገነዘበኝ ነው። ከህንዳውያን ጋር ብቻ ሳይሆን አብረን ከተጓዝን ጋዜጠኞች አንዱ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእናንተ የብቻ ሳይሆን እኛንም እንደራሳችን ሆኖ እያገለገለን ያለ የጋራ አየር መንገዳችን ነው" ሲል ነው የገለፀው። ይሄ ለእኔ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገር ኩራት ብቻ ሳይሆን መለያ ምልክትም ጭምር መሆኑን የተረዳሁበት አጋጣሚ ነው። በቀናት ቆይታዬ በእንግዳ አክባሪነታቸውና በለገሱን ፍቅርና እንክብካቤ ከአገሬ የራቅኩ ያህል ሳይሰማኝ ብቸኝነትን ሳላስተናግድ እንደውም እየናፈኳቸው እንድመለስ ላደረጉኝ ህንዳውያን በከበረ ሰላምታ ላመሰግን እወዳለሁ።
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 382
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል።   ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል።   የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው።   የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው።   ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።    
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 916
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች።   የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች።   ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ።   ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።      
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 1038
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 3227
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 2709
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 2905
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 4021
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2546
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2309
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3748
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48289
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43753
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 27996
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25343
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 23591
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 21734
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 21578
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 21204
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48289
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43753
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 27996
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25343
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በቻይና ይህም አለ!
Jul 8, 2025 75
  በአብነት ታደሰ በርግጥ ከዓለማችን የጥንት ስልጣኔ ምድሮች አንዷ ናት- ቻይና። በታሪክ ገጾች ‘የግኝት ምድር’(Land of Invention) የሚል ተቀፅላ የሰፈረላት የሺህ ዘመናት ባለታሪክ ሀገር። የጥንት ቻይኖች አያሌ ‘ግኝቶችን’ ለዓለም አካፍለዋል። ወረቀት ፈብርከው ዘመናቸውን ጽፈዋል፣ ማተሚያ ቁስ ፈጥረው አትመዋል፤ ኮምፓስ ፈልስመው አቅጣጫ ጠቁመዋል።በ221 ዓመተ-ዓለም አንድ ወጥ ስርወ መንግስት መስርተው በሀገረ መንግስት የታሪክ ዑደት ከፍታንም ዝቅታንም አይተዋል። በቻይና አያሌ ስርወ መንግስታት ተፈራርቀዋል። ቻይናውያን ክፉውንም ደጉንም ችለው አልፋዋል። የሕዝቡ ጽናት፣ ጥበብ፣ ቱባ ባህል፣ ታሪክና ብልሃት በቻይና ግንብ ይመሰላል። ግንቡም ዝም ብሎ የጡብ ክምር አይደለም፤ የመሰረተ-ጽኑነታቸው ትዕምርት(symbol) እንጂ። ሲሶውን ሕዝቧ በያንግትዝ ወንዝ ተፋሰስ ጉያ አቅፋ፣ ጥንተ ማንነቷን ሸክፋ ዕልፍ ዘመናትን ተሻግራለች። የቻይና ስርወ መንግስታት ከስመው የዛሬዋ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ ቻይና ከተመሰረተች ገና አንድ ምዕተ ዓመቷ ነው። ቅድመ ልደተ ክርስቶት በ221 ዓመተ-ዓለም የተመሰረተው ወጥ-ስርዎ መንግስት በመልከ ብዙ ምክንያቶች ተዳከመ። በፈረንጆቹ 1912 የመጨረሻው የቻይና ስርዎ መንግስት ተንኮታኮተ። ዘመናዊቷ የቻይና ሪፐብሊክ በዚህ ዘመን ተመሰረተች። ዳሩ ለውጡ አልጋ በአልጋ አልሆነም። ለሺህ ዘመን የጽኑ ስርዓተ መንግስት ባለቤቷ ሀገር ቻይና በአስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት ታመሰች። ወረራንም፣ ዕልቂትንም አስተናገደች። በዘመኑ ማኦ ዘዶንግ የሚባል ባለራዕይ መሪ በቻይና ምድር ተነሳ። አርቆ አሰበ፤ ሀሳቡንም አሰረጸ፤ በዓላማ ጸንቶ ክፉ ዘመን ተሻገረ። ማኦ እና ተከታዮቹ ለቻይና ትንሳኤ ታተሩ። በጽናት ታገሉ። ለመስዕዋትነት ቆርጠው ተነሱ፤ ዋጋም ከፈሉ። በአውሮፓዊኑ ዘመን አቆጣጣር በ1949 የዛሬዋን የቻይና ሕዝባዊ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ መሰረተ። ሃሳቡን ወደ ፖሊሲ ቀየረ፤ ተገበረውም። ቻይናን በኢንዱስትሪና ግብርና ምርት በንቅናቄ የማስፈንጠር ፕሮግራምንም (Great Leap Forward) ገቢራዊ አደረገ። ሆኖም ፖሊሲው በአንዴ ፍሬ አላፈራም። በወቅቱ በተፈጥሯዊና በሌሎች ምክንያቶች ቻይና በረሀብ ጠኔ ተመታች። ቻይናዊያን ተራቡ፤ ጎረቤት ሀገራትን ደጅ ጠኑ፤ ታላቁን ረሀብ መሻገር ያልቻሉ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቻይናዊያን በረሀብ አለቁ። በቻንግሻ የሚገኘው የማኦ ዘዶንግ ግዙፍ ሐውልት መራራ ጽዋን ተጎነጩ። የሀገሪቷ መሪ ማኦ ዘዶንግ በወቅቱ ፈተና ተስፋ ሳይቆርጥ ሀገር አሻጋሪ ፖሊሲውን ገቢራዊ አደረገ። ልመናን ለትውልድ ላለማውረስ፣ ንቅዘትን(ሙስናን) ነውር የሚያደርግ ስርዓት አጸና። ስራን ወንጌል፤ ሙስናን ወንጀል ያደረገ ጽኑ ስርዓተ መንግስት ገነባ። ከራሷ አልፋ ለዓለም የተረፈችዋን የዛሬዋን ቻይና በጽኑ መሰረት ላይ አነበረ። የዛሬዋ ቻይና ከዓለማችን ቁንጮ ልዕለ ሃያል ሀገራት አንዷ ናት። ከራሷ አልፋ ለዓለም ተርፋለች፤ የቻይና ቴክኖሎጂ ምጥቀትና ርቀት ዓለም ጉድ አሰኝቷል። በቅርቡ ሀገረ ቻይናን ከጎበኙ ጋዜጠኞች አንዷ ሆኜ ‘መልክዓ ቻይና’ን በወፍ በረር ቃኘሁ። በዚህ ማስታወሻዬ በቻይና የቴክኖሎጂ ልህቀትና ምጥቀት ላይ ብቻ አተኩራለሁ። ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ህዝብ ባላት፣ በ14 ሀገራት በምትዋሰነው፣ በአንድ ኮሚኒስት ፓርቲ በምትመራው ሀገር ቻይና በነበረኝ የ15 ቀናት ቆይታ ቻይና እንደ ጥንተ ታሪኳ ሁሉ በዘመኑ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ላይ ያላትን የመራቀቅ ጥግ ታዘብኩ። ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን የመቅደም እሽቅድድሟ ‘አጃይብ’ ያሰኛል። በሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና በማዕከላዊ ቻይዋ በምትገኘው የሁናን ግዛት ዋና ከተማ ቻንግሻ ምልከታዬ ቻይና ’ከተባለላት በላይ’ የቴክኖሎጂ ምጥቀቷ አስደንቆኛል። ምናልባትም የመጀመሪያ ጉዞዬ መሆኑም ነገሩን በአንክሮት እንድመለከት ሳያስገድደኝ አልቀረም። የሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከ22 ሚለዮን የሚልቅ ህዝብ በጉያዋ የታቀፈችው ታላቋ ቤጂንግ ከተማ ከዓለማችን ግንባር ቀደም የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህል፣ የቱሪዝምና የዲፕሎማሲ ማዕከላት አንዷ ናት። የአዲስ አበባ እህት ከተማ በዚህ ወቅት ሞቃታማ አየር ጸባት አላት። ቤጂንግ የ21ኛው ክፍል ዘመን የኪነ ህንፃና ክትመት ቴክኖሎጂ ያበበች ብቻ አይደለችም፤ ይልቁኑም በዛፎች ሀመልማላዊ ገጽታ የተላበሰች ውብ መዲና እንጂ። በሕንፃዎችም፣ በዛፎችም የተደነነች ከተማ። በተፈጥሮ የበቀሉ የሚመስሉ ሰማይ ታካኪ ሕንጻዎች፤ የመንገድ መሰረተ ልማት ስፋት፣ ጽዳትና ጥራት ‘ኩልል’ ያለች፣ ‘ምልል’ የምታደርግ ከተማ ያደርጋታል። ቤጂንግ ከተማ ከዘመናችን አስደናቂ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አንዱ በሆነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት(አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ) ሕይወትና ኑሮን እንዴት እንዳቃለለ የቤጂንግ የዕለት ከዕለት ክዋኔ ሁነኛ ማሳያ ነው። ቻይኖች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ተጠበዋል፤ መጠበብ ብቻም ሳይሆን ኑባሬያቸውን ሰው ሰራሽ አስተውሎት መር አድርገዋል። ከሮቦት መስተንግዶ እስከ ሰው ሰራሽ ፀሐይ መራቀቅ ይስተዋላል።   ካረፍኩበት ሆቴል (15ኛ ወለል ላይ ከሚገኘው መኝታ ክፍሌ) ሆኜ ያዘዝኩት ምግብ በቅጽበት አስተናጋጇ ‘ከች’ ብላ ትደውላለች። ፍጥነቷ ስትገረም፤ አስተናጋጆች ሮቦቶች መሆናቸውን ስትመለከት ይበልጥ ትደነቃለለህ። በክፍሌ ውስጥ ማብሪያ ማጥፊያ ስጫን መጋረጃው ሲከፈት መደንገጤን አልሸሽግም፣ ከምሽቱ 3 ሰዓት ፀሐይ አለመጥለቋን ስመለከት ‘የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ወጣች እንዴ?’ ማለቴ አልቀረም። በነገራችን ላይ የቻይና የሰው ሰራሽ ፀሐይ ሳይንሳዊ ፈጠራ ሁለት ግዜ ተሞክሮ ያለምንም እንከን እንደሚሰራ ነግረውናል። የሰው ሰራሽ ፀሐዩ ሃይድሮጅን እና ዱተሪየም ጋዞችን እንደ ሀይል ማመንጫ ነዳጅነት በመጠቀም ንጹህ ኢነርጂን ለማመንጨት ታስቦ ዲዛይን እንደተደረገና ሰው ሰራሽ ፀሐይ በርሐን ከተፈጥሮ ፀሐይ 13 እጥፍ ያክል ሙቀት እንደሚያመነጭም ሰምተን ተደንቀናል። የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ፕሮጀክት የሥራ ሰዓትን ከ13 ሰዓት ወደ 24 ሰዓት ለመጨመርና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብ የሰነቀ ነው። በቻይና በሰዉ ቅርፅ የተሰሩ ሮቦቶች በእግር ኳስ ጨዋታዎች ተወዳጅነት አትርፈዋል። ቤጂንግ የሚገኘው ሂዩማኖይድ የተሰኘ የሮቦት ቡድን የሰራቸው ሮቦቶች አመርቂ ውጤት ከራቀው የሀገሪቷ እግር ኳስ ቡድን ይልቅ የሀገሬውን ቀልብ እንደሳቡ ይነገራል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት በታገዘ የሮቦቶች ውድድር አያሌ ቻይናዊያን ይታደማሉ። ሮቦቶቹ በጨዋታ መሐል ቢወድቁ በራሳቸውን ይነሳሉ፤ ቢጎዱም ከሜዳ የሚወጡበት ስርዓት ተዘርግቷል። የታላቋ ቻይና ሰዎች ቴክኖሎጂን ከችግር መፍቻነት ወደ መዝናኛነትም አልቀውታል። በሀገራችን እንደ አዲስ ቴክኖሎጂ በንግዱ ስርዓት ውስጥ እየተዋወቀ ያለው የፈጣን ምላሽ መለያ ወይም ኪው አር ኮድ(Quick Response code) በቻይና ዕለታዊ ከዋኔዎች ቅንጦት አይደለም። በቻይና ማንኛውም ግልጋሎት በዚህ በዲጂታል ስርዓት ይከወናል። እንደሌሎች ስልጡን ሀገራት ሁሉ በንክኪ የሚደረግ ገንዘብ ዝውውር ቀርቷል። በቤጂንግ ጎዳናዎች በኪው አር ኮድ(QR Code) በሚንቀሳቀሱ ሞተር ሳይክሎችን በየመንገዱ ተሰድረዋል፤ የፈለገ መንገደኛ ሳይክሎችን በመጠቀም ወደ ፈለገበት ስፍራ ተንቀሳቅሶ ክፍያውን በኪው አር ኮድ ከፍሎ ይሄዳል። ሌላውም እንዲሁ። በአዲስ አበባ መኖሪያ ሰፈሬ የነበሩ ሳይክሎኝ ከደጃችን ደብዛቸው እንደጠፋ ሳስብ በቻይኖች ብልሃት፣ ታማኝነትና የከተሜነት ልህቀት ቀናሁ። በርግጥ በቻይና ኪው አር(QR) ኮድ ለተገለገልንበት መክፈያ ብቻ ሳይሆን ለልመናም መዋሉን ሲመለከቱ ፈገግ ሊሉ ይችላሉ። በቻይና ይህም አለ በማለት። በርግጥ በቤጂንግ የሰው እጅ ከሚያይ ይልቅ ጆሮቸውን ቢቆጥርጣቸው የሚሰሙ የማይመስሉ አዛውንቶች ሳይቀር በስራ ላይ ተጠምደው ይስተዋላሉ። ከቻይናውያን ጋር ለመግባባት በተለይም በንግድ ማዕከላት የቻይንኛ ቋንቋ መረዳት ግድ ይላል። “ሃው ማቺ፣ ጉዳ ጉዳ፤ ሺሼ፣ ኢ፣ አር…” እና መሰል ቃላት ማወቅ ይበጃል። ከዚህ ባለፈ በምልክት መግባባት አልያም በቋንቋ ተርጓሚ መተግበሪያ መጠቀም ያሻል። የቻይና ሰራሽ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምርቶች በራሳቸው ብራንድ፣ ቋንቋና መልክ እየተመረቱ በተመጣጣሽ ዋጋ ለህዝቦቿ ተደራሽ እየተደረጉ ነው። የቻይና የራስ-በቅነት ጥረት ያስቀናል። በቴክኖሎጂ፣ በባሕልና በኢኮኖሚ ተጽዕኖ ተላቀው በራሳቸው ለመቆም የሄዱበት ርቀት ግሩም ነው። ግብይቶች በራሳቸው ገንዘብ ብቻ ይከወናል። በወቅቱ ምንዛሬ አንድ የአሜሪካ ዶላር ሰባት የቻይና ገንዘብ(ዩዋን) ነው። ከምዕራባዊያን ማህበራዊ ትስስር ገጾች(ለምሳሌ ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ፣ ቲክቶክ) በሕግ በማገድ የራሳቸውን መተግበሪያ አበልጽገው ገቢራዊ አድርገዋል። ‘ዊቻት’ የተሰኘው መተግበሪያ ሁሉም ቻይናውያን መገልገያ ነው።   ከቤጂንግ ሌላ ያስደነቀችኝ ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከተማ ነች። ቻንግሻ ስመ-ብዙ ነች። ከሶስት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ ጠገቧ የሁናን ግዛት ርዕሰ መዲና ቻንግሻ ‘የከዋክብት ከተማ’ ትሰኛለች። በነገራችን ላይ ማኦ ዘዶንግ ትውልዱ ሁናን ግዛት ውስጥ ነው። ቻንግሻ በስራ ከተማነቷ ‘የማታንቀላፋው መዲና’ ትባላለች። በመዝናኛ ስፍራነቷ ‘የተዝናኖት መነሃሪያ’ የሚል ተቀጥላ ስም አላት። ‘የሚዲያ ጥበብ’ ስፍራም ትሰኛለች። በኢንዱስትሪ፣ በጥንታዊ ሐውልቶች፣ አብያተ መቅደሶች፣ ታሪካዊ ስፍራዎች መገኛ በመሆኗ በቱሪስቶች ተወዳጅ ከተማ ናት። ትናንትና ዛሬን ያዋደደች፣ ታሪክና ባህል ባዛነቀችዋ ቻንግሻ የአምስት ቀናት ቆይታዬ ብዙ ገጽታዋ አስደምሞኛል። የሻንግ ወንዝን ተንተርሳ፣ በተራራማ፣ በሜዳማና ኮረብታማ መልክዓ ምድር በማዛነቅ የተቆረቆረች በመሆኗ የስብት ማዕከል ሆናለች። እንደ ቤጂንግ በደን የተከበበች፣ በዘመነኛ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች እና በታሪካዊ ኪነ ሕንጻዎች የተጌጠች ከተማ ናት። ከዚህ ባሻገር የአምራች ኢንዱስትሪዎች መናገሻም ናት። የምቹ ከተሜነትና ጠንካራ የስራ ባህል በግላጭ የሚስተዋልባት ከተማ። የዓለማችን ገዙፉ በጣም ሞቃታማ አየር ጸባይ ባላት ቻንግሻ ሌት ከቀን ይሰራል። ፋብሪካዎቿ አይተኙም። ሌትና ቀኑ የሚታወቀው በሰዓት ብቻ እንጂ የስራና የንግድ ድባቡ እኩል ነው። ብርሃናማዋ ቻንግሻ ‘የቻይዊያን መስቀል’ በተሰኘው በቀይ በተቀለመው መስቀልም ትታወቃለች። በርግጥ ከዓለማችን ግዙፍ ማማዎች አንዱ የሆነው ሕንጻም መገኛ ናች። በጥቅሉ የቻይና ጉብኝት ትዝብቴ የገናና ታሪክ ባለቤቷ ሀገር ከባድ ውጣ ውረዶችን አልፋ ዛሬ ዓለምን እየቀደመች መሆኑን ሳስብ፤ እንደቻይና ሁሉ የሺ ዘመናት ገናና ታሪክና አኩሪ ገድል ያላት ኢትዮጵያስ የሚል ተጠየቅ እንዳውጠነጥን አድርጎኛል። ቻይናዊያን የዘመን የፈተና ቋጠሮዎቻቸውን ፈታተው ከዛሬ ከፍታ ሰገነት ላይ ወጥተዋል። ከዛሬም በበለጠ ነገን በጽኑ መሰረት ላይ እየገነቡ ነው። እኛስ? ብዬ ሳስብ በቁጭትና በተስፋ ተዋጥኩ! ሰላም!
በ17ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ መሪዎቹ ምን አሉ?
Jul 7, 2025 109
በ17ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ መሪዎቹ ምን አሉ? 17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ እየተካሄደ ይገኛል ጉባኤው እየተካሄደ የሚገኘው “ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የደቡብ ንፍቀ ዓለም” በሚል መሪ ሀሳብ ነው። በጉባኤው ላይ ተሳታፊ የሆኑ የብሪክስ አባል እና አጋር ሀገራት መሪዎች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች በዓለም አንገብጋቢ እና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሀሳባቸውን ሰንዝረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ብሪክስ ከጠንካራ አዲስ ሀሳብ ተነስቶ ለዓለም አቀፍ ለውጥ የሚሰራ ብርቱ ኃይል ወደመሆን ተሸጋግሯል። ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የጋራ ደኅንነትን እና ሁሉን አካታች ብልጽግናን ለማምጣት በሚያስችል ሁኔታ አፋጣኝ ማሻሻያ ማድረግ አለባቸው። በብሪክስ አዳዲስ አባላት መጨመራቸው የጋራ ድምፃችን የበለጠ ይጠናከራል። የጋራ አላማችን የበለጠ ይጠራል። አቅማችንም ይሰፋል። እንደ ብሪክስ አባልነቷ ኢትዮጵያ እነዚህ ጥረቶች እንዲሳኩ በተለይም በአለምአቀፍ ውሳኔ ሰጪ መድረኮች ለአዳዲስ ገበያዎች እና በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት ሰፋ ያለ ውክልና በሚገኝበት ሁኔታ ላይ በንቃት አስተዋፅኦ ታደርጋለች። የብራዚል ፕሬዝዳንት ሉዊስ ኢግናሲዮ ሉላ ዳ ሲልቫ የዓለምን የአስተዳደር ስርዓትን ለመቀየር የሚያስችል መሰረተ ልማትና የጋራ ትብብራችንን ማጠናከር ይገባል። ብሪክስ ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚሆን አዲስ የብዝሃ ዓለም አስተዳደር የመፍጠር ቁልፍ ሚና አለው። ከጦርነት ይልቅ ሰላም ላይ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ትርፋማ ያደርጋል። የበለጸጉ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ቃል የገቡትን ገንዘብ መስጠት አለባቸው። የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ ብሪክስ በዓለም ፍትሃዊ እና መርህን ያከበረ የዓለም ስርዓት እንዲፈጠር የመሪነት ሚናውን መወጣት አለበት። ለብሪክስ ሀገራት የኢኮኖሚ እድገት ልማት ትልቅ ድርሻ ያለው የእድገት ምሰሶ ነው። በብሪክስ ሀገራት መካከል ያለውን የባህል ልውውጥ እና የጋራ መማማር የበለጠ ማሳደግ ይገባል። ብሪክስ በዓለም ደረጃ ያሉ ግጭቶች በውይይት እና በንግግር እንዲፈቱ በማድረግ የሰላም ኃይል መሆኑን በተጨባጭ ማሳየት ይኖርበታል። የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን (በበይነ መረብ) ሊበራሊዝም መር የሆነው የዓለም የሉላዊነት አስተዳደር ስርዓት ጊዜው አልፎበታል፤ አዲስ የባለብዝሃ የዓለም ስርዓት እያቆጠቆጠ ነው። በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት በራሳቸው ገንዘብ የመገበያያት ልምምዳቸውን ማጠናከር አለባቸው። የብሪክስ ሀገራት በተፈጥሮ ሀብት፣ ሎጅስቲክስ፣ ንግድ፣ ፋይናንስ እና በሌሎች መስኮች ያላቸውን ትብብር ማጠናከር አለባቸው። በሚሸፍነው መልክዐ ምድር፣ በያዘው የህዝብ ብዛት እና በዓለም ኢኮኖሚ ውስጥ ባለው ድርሻ ብሪክስ ትልቅ ኃይል ሆኗል። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ዓለም አቀፍ ተቋማት የደቡብ ንፍቀ ዓለምን ፍትሃዊ ውክልና በሚያረጋገጥ መልኩ ሁሉን አቀፍ ሪፎርም ሊደረግበት ይገባል። የ21 ክፍለ ዘመን ሶፍትዌር በ20ኛ ክፍለ ዘመን የታይፕ ራይተር ማሽን ላይ ግልጋሎት ሊሰጥ አይችልም። የሰው ልጅ እና የዓለማችን የምንግዜውም ትልቅ ስጋት ሽብርተኝነት ነው። ሽብርተኝነት መከላከል እና ማውገዝ የሁሉም የጋራ ኃላፊነት ነው። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ መጠቀም እና ማስተዳደር በጣም አስፈላጊ ነው። ህንድ በዓለም ደረጃ ያሉ አለመግባባቶች በዲፕሎማሲ፣ በሰላም እና በንግግር እንዲፈቱ በቁርጠኝነት ትሰራለች። የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ስሪል ራማፎሳ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ወቅታዊ የዓለም ነባራዊ ሁኔታን መሰረት ያደረገ አፋጣኝ ማሻሻያ ያስፈልገዋል። ብሪክስ ዓለም አቀፍ የጂኦ ፖለቲካ ውጥረቶችን ለመፍታት፣ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን እና አሳታፊ የደህንነት ማዕቀፎችን ማረጋገጥ የሚያስችል የጋራ አሰራር መፍጠር አለባቸው። ደቡብ አፍሪካ የብሪክስ የፀረ-ሽብርተኝነት ስትራቴጂ ውጤታማ በሆነ ሁኔታ ለመተግበር ቁርጠኛ ናት። የብሪክስ መስፋት ንግድ ፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች አዳዲስ የትብብር አማራጮችን ይፈጥራል። የኢንዶኔዥያ ፕሬዝዳንት ብራቦዎ ሱቢያንቶ ብሪክስ በደቡብ-ለደቡብ ሰላም፣ ደህንነት፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ የዓለም ጤና እና የከባቢ አየር ትብብር ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡ የዓለም የብዝሃ ወገን ተቋማት እኩልነትን ይበልጥ የሚያረጋግጥ ለውጥ ያስፈልጋቸዋል። በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ አማካኝነት በብሪክስ እና በምዕራቡ ዓለም መካከል ሚዛናዊ ትብብር መፍጠር ይገባል። በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ኢ-ፍትሃዊ አካሄድ እና ጦርነት እንደ አማራጭ መጠቀም ሊቆም ይገባል። ዓለም አቀፍ ፍትህ እና ሰላምን ማስፈን ጊዜ ሊሰጠው የማይገባ ጉዳይ ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዓለም ከምንጊዜውም በላይ ሰላም ያስፈልጋታል። ግጭቶችን በውይይት እና በንግግር መፍታት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። የሰውን ህይወት እና ኢኮኖሚ በፍጥነት እየቀየረ ያለውን የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለእኩይ አላማ እንዳይውል በከፍተኛ ኃላፊነት እና ጥንቃቄ መጠቀም ይገባል። ብዝሃ ዓለም የባለብዝሃ ወገን አስተዳር ስርዓት ያስፈልገዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት እና የዓለም የፋይናንስ መዋቅርን ጨምሮ የዓለም የአስተዳደር ስርዓት ከጊዜው ጋር ተራማጅ መሆን አለበት። በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት በዓለም ኢኮኖሚ እና አስተዳደር ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ የበለጠ ማሳደግ ይገባል። ሁለተኛ ቀኑን የያዘው 17ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም