ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በክልሉ ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ ለልማትና ለመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል
Jul 16, 2026 44
ቡታጅራ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል። የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ ተግባቦት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ነው።   በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ የክልሉን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝብን የልማትና የመልካም እስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ፡፡ በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የዘርፉ አመራር ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ጠቅሰዋል፡፡ የገቢ አሰባሰብ ስራውን በልዩ ድጋፍና ክትትል በመምራት በዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በማረም በክልሉን ፈጣን እድገት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡   የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቀመሪያ ረሻድ በበኩላቸው ለክልሉ ህዝብ የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ገቢን በአግባቡ የመሰብሰብ ስራው በልዩ በትኩረት እየተመራ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ኃላፊዋ ገለጻ በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት 27 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 26 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰብ ተችሏል። ገቢው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ9 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ጠቅሰው ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ የተፈጠረው ግንዛቤ፣ የገቢ አሰባሰቡ ወጥ በመደረጉ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ መሰራቱ እና የድጋፍና ክትትል ስርዓት መጠናከሩ ለገቢው መጨመር አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በተጀመረው የ2019 በጀት ዓመት 35 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማሰባሰብ መታቀዱንና ይህንንም ለማሳካት የግብር ህጉን የማስከበር እና በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።        
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአፍሪካ ደረጃ በአርዓያነት የሚጠቀስ ተቋም ነው
Jul 16, 2026 58
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአፍሪካ ደረጃ በአርዓያነት የሚጠቀስ ተቋም መሆኑን የአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል፡፡ የአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ በዚሁ ጊዜ፣ ተቋሙ በአህጉር ደረጃ ሞዴል መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ ሰፊ የለውጥ ጉዞ በማድረግ በአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ከሚታመኑባቸው የልህቀት ማዕከላት አንዱ መሆን ችሏል ብለዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ ወረርሽኞችን አስቀድሞ በመከላከል እንዲሁም ሲከሰቱ በፍጥነት በመቆጣጠር ረገድ የገነባው አቅም ለሌሎች አፍሪካውያን አገራት ትልቅ አርአያ መሆኑን አድንቀዋል። በአፍሪካ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የነበራቸው አገራት በቁጥር 12 ብቻ የነበሩ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 40 ማደጋቸውን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ፣ ለዚህ ዕድገት የኢትዮጵያ ተሞክሮ ትልቅ ሚና እንደነበረው ተናግረዋል። አህጉሪቱ በቀጣይ የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት ያላቸውን አገራት ቁጥር ወደ 50 ለማድረስ ግብ የጣለች ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዚህ ሂደት ውስጥ እንደ ዋና ሞዴል እንደምታገለግል አስረድተዋል። በአፍሪካ ጠንካራ የላቦራቶሪ ትስስር መኖር የሕብረተሰብ ጤና ሥራዎችን ለመከወን ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ማዕከሉ ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር የላቦራቶሪ ትስስር መረብ ለመገንባት ሥራ መጀመሩን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያም የዚህ የሙከራ ትግበራ መነሻ ከሆኑት ቀዳሚ አገራት አንዷ መሆኗን ገልጸዋል። የአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በቅርበትና በተቀናጀ መልኩ ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያንም በኢንስቲትዩቱ ባስመዘገበው ውጤትና በደረሰበት የልህቀት ደረጃ ሊኮሩ እንደሚገባ ጠቅሰዋል፡፡    
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓትና የላብራቶሪ አቅም ገንብታለች- ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ
Jul 16, 2026 55
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓትና የላብራቶሪ አቅም የገነባች ሀገር መሆኗን በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ ገለፁ። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በተገኙበት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ ይገኛል።   በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ በዚሁ ወቅት፥ ኢንስቲትዩቱ ባለፈው አንድ ክፍለ ዘመን በሕብረተሰብ ጤና ዘርፍ ላስመዘገባቸው ታላላቅ ስኬቶች አድናቆታቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን በሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች አስተዳደር ረገድ የዓለም ጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል አድርጎ ለመሰየም የሚያስችል የድጋፍ ደብዳቤ በቅርቡ ለጤና ሚኒስቴር እንደሚላክም ይፋ አድርገዋል። በተጨማሪም የኢንስቲትዩቱ የአደጋ ጊዜ አስተዳደር ቡድን ዓለም አቀፍ የእውቅና ማረጋገጫ የማግኘት ሂደት የጀመረ ሲሆን ይህ ሂደት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያገኘ የአደጋ ጊዜ አስተዳደር ቡድን ያላት ሁለተኛዋ የአፍሪካ ሀገር ትሆናለች ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ የቅኝት፣የላብራቶሪ፣ ምርምር፣ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትና ምላሽ እንዲሁም በማስረጃ ላይ የተመሠረተ የፖሊሲ ቀረጻን በማቀናጀት የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓት መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ግንባር ቀደም እና ጠንካራ ከሆኑ የሕብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ሥርዓቶች አንዱን መገንባት ችላለች ብለዋል። በቅርቡ የተከሰተውን የማርበርግ ወረርሽኝ በመከላከል ረገድ ኢትዮጵያ ፈጣንና ውጤታማ ምላሽ በመስጠት ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ችላለች ሲሉ ጠቅስዋል። የኢንስቲትዩቱ የዳበረ ልምድና የባለሙያዎች ብቃት አሁን ላይ ከኢትዮጵያ አልፎ ለሌሎች ጎረቤት ሀገራት በቴክኒክ ትብብር፣ በላብራቶሪ አገልግሎትና በሕብረተሰብ ጤና አመራር ዘርፍ ከፍተኛ ድጋፍ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 11 ቀን 1947 የዓለም ጤና ድርጅት መስራች አባል በመሆን በይፋ የተቀላቀለች ሲሆን ባለፉት 79 ዓመታት ከድርጅቱ ጋር በመሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የጤና ሥርዓትን በመቅረጽ ረገድ ጉልህ ሚና ስትጫወት መቆየቷን አስታውሰዋል። ከሁሉም ስኬቶች ጀርባ ያለው የኢትዮጵያ ትልቁ ሀብት ሕዝቧና በኤፒዲሚዮሎጂ፣ በላብራቶሪ ሳይንስና በአደጋ ጊዜ አስተዳደር ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል ነው ሲሉ ተናግረዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፣ አዳዲስና ዳግም የሚቀሰቀሱ በሽታዎች፣ የጸረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች መላመድ እና ሰብአዊ ቀውሶች የወደፊቱን የጤና ገጽታ እየቀየሩት መሆኑን ጠቅሰዋል። እነዚህን ለመቋቋም እንደ ኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ያሉ ተቋማትን ማጠናከር፣ ጠንካራ አጋርነት መፍጠርና የማይበገሩ የጤና ሥርዓቶችን መገንባት የግድ ይላል ብለዋል። የዓለም ጤና ድርጅት ኢንስቲትዩቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፣ የዲጂታል ጤና ሥርዓትን ለማስፋፋትና ዓለም አቀፍ የጤና ደንቦችን ተግባራዊ ለማድረግ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና የብሔራዊ ደህንነት ዋነኛ መሰረት መሆኑን በጽኑ ያምናል-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ
Jul 16, 2026 101
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግስት የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና የብሔራዊ ደህንነት ዋነኛ መሰረት መሆኑን በጽኑ ያምናል ሲሉ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በተገኙበት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል። ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለዜጎች ጤንነትና ለሀገር ደህንነት ያለው ሚና ወሳኝ ነው፡፡ የኢንስቲትዩቱ የመቶ ዓመት ጉዞ ኢትዮጵያ ለዜጎቿ ጤና የምታደርገው ጥረትና የጤና ሥርዓት ግንባታ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። የሀገር ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ደህንነት ከህብረተሰብ ጤና ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳለው ጠቅሰው፥ የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ ጥንካሬ የወደፊት እርምጃዋ በዜጎቿ ጤና መጠበቅ ላይ የተመሠረተ ነው ብለዋል፡፡ በዚህ ሂደት የሕክምና ምርምር አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ፈታኝ የሆኑ ዓለም አቀፋዊ የጤና ቀውሶችን፣ ወረርሽኞችንና የተላላፊ በሽታዎችን በመከላከል ረገድ ያሳየው አፈጻጸም የሚደነቅ ነው ሲሉም ተናግረዋል። በተለይም እንደ ኮቪድ-19፣ ኤምፖክስ እና ማርበርግ ባሉ ወረርሽኞች ወቅት ኢንስቲትዩቱ ያሳየው ፈጣን ምላሽና ሳይንሳዊ አመራር ለሀገሪቱ ክብርን ያጎናጸፈ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማት፣የኢኮኖሚ ዕድገትና የብሔራዊ ደህንነት ዋነኛ መሠረት መሆኑን በጽኑ ያምናል ነው ያሉት ፕሬዝዳንት ታዬ። መንግሥት ጠንካራ ተቋማትን የሀገር ግንባታ መሠረት አድርጎ እንደሚመለከት በማስታወስ፣ ለኢንስቲትዩቱ የመሠረተ ልማትና የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል። ኢንስቲትዩቱ ለወደፊቱ ይበልጥ ውጤታማና ተወዳዳሪ እንዲሆን መንግሥት አመቺ የፖሊሲ መደላድልን እንደሚፈጥርም ተናግረዋል። ባለፉት ስኬቶች ላይ በመመሥረት የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን የመከላከልና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅምን ማዘመን እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተጨማሪም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የበሽታዎችን ስርጭት አስቀድሞ መተንበይ የሚያስችል ፈጣንና ዘመናዊ መረጃ አያያዝና ትንተና ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባም ጠቅሰዋል። የኢንስቲትዩቱ መቶኛ ዓመት የምስረታ በዓል ያለፈውን የሚዘክርበት፣ የአሁኑን የሚያመሰግኑበትና ለወደፊቱ የላቀ ዕቅድ የሚያቅዱበት መሆኑንም ገልጸዋል። የኢንስቲትዩቱ የፅናት፣ የእድሜና የህልውና ሚስጥር የሚቀዳው ከሰራተኞቹና ከተመራማሪዎቹ ጥንካሬ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ መንግሥት ለኢንስቲትዩቱ ተልዕኮ መሳካት ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በ100 ዓመታት ለዜጎች የጤና ጥበቃ ውጤታማ ዘመን የማይሽረው አሻራ አሳርፏል
Jul 16, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለፉት 100 አመታት ለዜጎች ጤና ጥበቃ ውጤታማነት ዘመን የማይሽረው የጥናትና ምርምር አሻራ ማሳረፉን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ገለጹ። ኢንስቲትዩት የ100ኛ በዓሉን ከዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያከብራል።   የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት፣ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል። በክብረ በዓሉ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ (ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባን ጨምሮ የአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት 100 ዓመታት ለኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ጥበቃና ደኅንነት ዘርፎች ውጤታማ ሳይንሳዊ የጥናትና ምርምር ተግባራትን በማከናወን፣ ዘመን የማይሽረው ታሪካዊ አሻራ አሳርፏል። ኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ቀድሞ በመለየትና ምርምር በማካሄድ፣ የተለያዩ ክትባቶችን በማምረት እንዲሁም ለጤና አደጋዎች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ረገድ ውጤታማ ሲሆን መቆየቱን ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ የጤና ፖሊሲና ስትራቴጂ ቀረጻ ላይ ሳይንሳዊ የጥናት ውጤቶችን እንደ ግብዓት በማቅረብ፣ የሚከሰቱ ወረርሽኞችን ቀድሞ በማወቅ፣ በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ጥራት ያለው የላብራቶሪ ምርመራ ሥርዓት በመዘርጋት እንዲሁም የሙያተኞችን አቅም በመገንባት ውጤታማ ተግባራትን እንዳከናወነ አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም ወረርሽኞችን አስቀድሞ የመተንበይና የመረጃ ፍሰትን የማዘመንና የማሳደግ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ኢንስቲትዩቱን በምሥራቅ አፍሪካ የሕዝብ ጤና ምርምርና ስልጠና ግንባር ቀደም ተቋም ለማድረግ ራዕይ ሰንቆ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ የ100ኛ ዓመት በዓሉን ከዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያከብራል።
የሚታይ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓትና የላብራቶሪ አቅም ገንብታለች- ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ
Jul 16, 2026 55
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓትና የላብራቶሪ አቅም የገነባች ሀገር መሆኗን በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ ገለፁ። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በተገኙበት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ ይገኛል።   በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ በዚሁ ወቅት፥ ኢንስቲትዩቱ ባለፈው አንድ ክፍለ ዘመን በሕብረተሰብ ጤና ዘርፍ ላስመዘገባቸው ታላላቅ ስኬቶች አድናቆታቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን በሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች አስተዳደር ረገድ የዓለም ጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል አድርጎ ለመሰየም የሚያስችል የድጋፍ ደብዳቤ በቅርቡ ለጤና ሚኒስቴር እንደሚላክም ይፋ አድርገዋል። በተጨማሪም የኢንስቲትዩቱ የአደጋ ጊዜ አስተዳደር ቡድን ዓለም አቀፍ የእውቅና ማረጋገጫ የማግኘት ሂደት የጀመረ ሲሆን ይህ ሂደት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያገኘ የአደጋ ጊዜ አስተዳደር ቡድን ያላት ሁለተኛዋ የአፍሪካ ሀገር ትሆናለች ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ የቅኝት፣የላብራቶሪ፣ ምርምር፣ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትና ምላሽ እንዲሁም በማስረጃ ላይ የተመሠረተ የፖሊሲ ቀረጻን በማቀናጀት የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓት መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ግንባር ቀደም እና ጠንካራ ከሆኑ የሕብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ሥርዓቶች አንዱን መገንባት ችላለች ብለዋል። በቅርቡ የተከሰተውን የማርበርግ ወረርሽኝ በመከላከል ረገድ ኢትዮጵያ ፈጣንና ውጤታማ ምላሽ በመስጠት ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ችላለች ሲሉ ጠቅስዋል። የኢንስቲትዩቱ የዳበረ ልምድና የባለሙያዎች ብቃት አሁን ላይ ከኢትዮጵያ አልፎ ለሌሎች ጎረቤት ሀገራት በቴክኒክ ትብብር፣ በላብራቶሪ አገልግሎትና በሕብረተሰብ ጤና አመራር ዘርፍ ከፍተኛ ድጋፍ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 11 ቀን 1947 የዓለም ጤና ድርጅት መስራች አባል በመሆን በይፋ የተቀላቀለች ሲሆን ባለፉት 79 ዓመታት ከድርጅቱ ጋር በመሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የጤና ሥርዓትን በመቅረጽ ረገድ ጉልህ ሚና ስትጫወት መቆየቷን አስታውሰዋል። ከሁሉም ስኬቶች ጀርባ ያለው የኢትዮጵያ ትልቁ ሀብት ሕዝቧና በኤፒዲሚዮሎጂ፣ በላብራቶሪ ሳይንስና በአደጋ ጊዜ አስተዳደር ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል ነው ሲሉ ተናግረዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፣ አዳዲስና ዳግም የሚቀሰቀሱ በሽታዎች፣ የጸረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች መላመድ እና ሰብአዊ ቀውሶች የወደፊቱን የጤና ገጽታ እየቀየሩት መሆኑን ጠቅሰዋል። እነዚህን ለመቋቋም እንደ ኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ያሉ ተቋማትን ማጠናከር፣ ጠንካራ አጋርነት መፍጠርና የማይበገሩ የጤና ሥርዓቶችን መገንባት የግድ ይላል ብለዋል። የዓለም ጤና ድርጅት ኢንስቲትዩቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፣ የዲጂታል ጤና ሥርዓትን ለማስፋፋትና ዓለም አቀፍ የጤና ደንቦችን ተግባራዊ ለማድረግ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና የብሔራዊ ደህንነት ዋነኛ መሰረት መሆኑን በጽኑ ያምናል-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ
Jul 16, 2026 101
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግስት የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና የብሔራዊ ደህንነት ዋነኛ መሰረት መሆኑን በጽኑ ያምናል ሲሉ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በተገኙበት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል። ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለዜጎች ጤንነትና ለሀገር ደህንነት ያለው ሚና ወሳኝ ነው፡፡ የኢንስቲትዩቱ የመቶ ዓመት ጉዞ ኢትዮጵያ ለዜጎቿ ጤና የምታደርገው ጥረትና የጤና ሥርዓት ግንባታ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። የሀገር ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ደህንነት ከህብረተሰብ ጤና ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳለው ጠቅሰው፥ የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ ጥንካሬ የወደፊት እርምጃዋ በዜጎቿ ጤና መጠበቅ ላይ የተመሠረተ ነው ብለዋል፡፡ በዚህ ሂደት የሕክምና ምርምር አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ፈታኝ የሆኑ ዓለም አቀፋዊ የጤና ቀውሶችን፣ ወረርሽኞችንና የተላላፊ በሽታዎችን በመከላከል ረገድ ያሳየው አፈጻጸም የሚደነቅ ነው ሲሉም ተናግረዋል። በተለይም እንደ ኮቪድ-19፣ ኤምፖክስ እና ማርበርግ ባሉ ወረርሽኞች ወቅት ኢንስቲትዩቱ ያሳየው ፈጣን ምላሽና ሳይንሳዊ አመራር ለሀገሪቱ ክብርን ያጎናጸፈ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማት፣የኢኮኖሚ ዕድገትና የብሔራዊ ደህንነት ዋነኛ መሠረት መሆኑን በጽኑ ያምናል ነው ያሉት ፕሬዝዳንት ታዬ። መንግሥት ጠንካራ ተቋማትን የሀገር ግንባታ መሠረት አድርጎ እንደሚመለከት በማስታወስ፣ ለኢንስቲትዩቱ የመሠረተ ልማትና የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል። ኢንስቲትዩቱ ለወደፊቱ ይበልጥ ውጤታማና ተወዳዳሪ እንዲሆን መንግሥት አመቺ የፖሊሲ መደላድልን እንደሚፈጥርም ተናግረዋል። ባለፉት ስኬቶች ላይ በመመሥረት የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን የመከላከልና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅምን ማዘመን እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተጨማሪም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የበሽታዎችን ስርጭት አስቀድሞ መተንበይ የሚያስችል ፈጣንና ዘመናዊ መረጃ አያያዝና ትንተና ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባም ጠቅሰዋል። የኢንስቲትዩቱ መቶኛ ዓመት የምስረታ በዓል ያለፈውን የሚዘክርበት፣ የአሁኑን የሚያመሰግኑበትና ለወደፊቱ የላቀ ዕቅድ የሚያቅዱበት መሆኑንም ገልጸዋል። የኢንስቲትዩቱ የፅናት፣ የእድሜና የህልውና ሚስጥር የሚቀዳው ከሰራተኞቹና ከተመራማሪዎቹ ጥንካሬ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ መንግሥት ለኢንስቲትዩቱ ተልዕኮ መሳካት ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በ100 ዓመታት ለዜጎች የጤና ጥበቃ ውጤታማ ዘመን የማይሽረው አሻራ አሳርፏል
Jul 16, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለፉት 100 አመታት ለዜጎች ጤና ጥበቃ ውጤታማነት ዘመን የማይሽረው የጥናትና ምርምር አሻራ ማሳረፉን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ገለጹ። ኢንስቲትዩት የ100ኛ በዓሉን ከዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያከብራል።   የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት፣ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል። በክብረ በዓሉ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ (ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባን ጨምሮ የአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት 100 ዓመታት ለኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ጥበቃና ደኅንነት ዘርፎች ውጤታማ ሳይንሳዊ የጥናትና ምርምር ተግባራትን በማከናወን፣ ዘመን የማይሽረው ታሪካዊ አሻራ አሳርፏል። ኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ቀድሞ በመለየትና ምርምር በማካሄድ፣ የተለያዩ ክትባቶችን በማምረት እንዲሁም ለጤና አደጋዎች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ረገድ ውጤታማ ሲሆን መቆየቱን ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ የጤና ፖሊሲና ስትራቴጂ ቀረጻ ላይ ሳይንሳዊ የጥናት ውጤቶችን እንደ ግብዓት በማቅረብ፣ የሚከሰቱ ወረርሽኞችን ቀድሞ በማወቅ፣ በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ጥራት ያለው የላብራቶሪ ምርመራ ሥርዓት በመዘርጋት እንዲሁም የሙያተኞችን አቅም በመገንባት ውጤታማ ተግባራትን እንዳከናወነ አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም ወረርሽኞችን አስቀድሞ የመተንበይና የመረጃ ፍሰትን የማዘመንና የማሳደግ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ኢንስቲትዩቱን በምሥራቅ አፍሪካ የሕዝብ ጤና ምርምርና ስልጠና ግንባር ቀደም ተቋም ለማድረግ ራዕይ ሰንቆ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ የ100ኛ ዓመት በዓሉን ከዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያከብራል።
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሀገር አልፎ የአህጉራችን ኩራት ነው- ዶክተር መቅደስ ዳባ
Jul 16, 2026 108
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሀገር አልፎ የአህጉራችን ኩራት ነው ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉ አከባበር ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢፌድሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ እና የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዓለም አቀፍ የጤና ዘርፍ ተወካዮችና አጋር አካላት ተገኝተዋል፡፡   የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፥ ኢንስቲትዩቱ ላለፉት አንድ መቶ ዓመታት በሀገሪቱ የጤና ታሪክ ውስጥ ጉልህና ታሪካዊ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል። በኢንስቲትዩቱ ውስጥ የሚገኙ ተመራማሪዎች፣ የቅኝት ባለሙያዎች፣ የመረጃ ተንታኞች፣ የአደጋ ምላሽ ሰጪዎች እና የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች የሚጫወቱትን የላቀ ሚና አድንቀዋል። ተቋሙ ሀገሪቱ አስቸጋሪ የጤና ፈተናዎችን ባለፈችባቸው ወቅቶች ያሳየው ተጋድሎ ትልቅና የሚደነቅ እንደነበር አስታውቀዋል። በተለይ በኮቪድ-19 እና በተለያዩ አስጊ ወረርሽኞች ወቅት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በቅርበት በመተባበር የሰራውን ውጤታማ ስራ አንስተዋል። የላብራቶሪ ምርመራና የቅኝት ስራዎችን በበላይነት መምራቱን፣ እንዲሁም በሳይንሳዊ ትንተናዎች የታገዘ ፈጣን የድንገተኛ አደጋ ምላሽ በመስጠት ግንባር ቀደም ሚና መጫወቱን አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አቅም በአሁኑ ወቅት ከሀገር ወሰን ማለፉን የገለጹት ሚኒስትሯ፣ ተቋሙ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካም ጭምር ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ የሚገኝ አህጉራዊ ኩራት መሆኑን አስገንዝበዋል። መንግሥት የጤናውን ዘርፍ ፍትሐዊነት ለማረጋገጥና ጥራትን ለማሻሻል በዋናነት በርካታ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ከገጠር እስከ ከተማ የጤና አገልግሎቶችን ማስፋፋት፣የእናቶችንና ህጻናትን ጤና ማሻሻል እንዲሁም ተላላፊና ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የሕዝቡን ተሳትፎ ማሳደግና ዜጎች በጤና ወጪ ምክንያት ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እንዳይጋለጡ ለማድረግ የባለቤትነት ስሜት በመፍጠር የማኅበረሰብ አቀፍ የጤና መድንን የማስፋፋት ሰፊ ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። ዓለም አዲስና ውስብስብ የጤና ሥጋቶች እንዳሉባት እያየን ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ እነዚህን ውስብስብ ሥጋቶች ለመመከት አደጋን አስቀድሞ የሚለይ፣ በፍጥነት የሚያስጠነቅቅ፣ በሳይንስ የሚተነትንና በተቀናጀ መልኩ ምላሽ የሚሰጥ ጠንካራ ተቋማዊ አቅም መገንባት መሆኑን በአጽንኦት ተስጥቶ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተልዕኮዎቹን በታማኝነትና በብቃት መወጣት እንዲችል ጤና ሚኒስቴር አስፈላጊውን የፖሊሲ፣ የአመራርና የአቅም ግንባታ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አገልግሎቱ የአሰራር ሥርዓቱን በማዘመን ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል
Jul 16, 2026 154
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዘመኑን የሚመጥን የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋፋት፣ የአሰራር ሥርዓቱን በማዘመን እና ምቹ የስራ ከባቢን በመፍጠር የተገልጋዩን እርካታ የሚያሳድጉ ተጨባጭ ለውጦች ማምጣቱን ዋና ዳይሬክተሯ ሰላማዊት ዳዊት ገለጹ፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት፤ ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።   በመግለጫቸውም፥ተቋሙ ዘመኑን የሚመጥን የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋፋት፣ የአሰራር ሥርዓቱን በማዘመን እና ምቹ የስራ ከባቢን በመፍጠር የተገልጋዩን እርካታ የሚያሳድጉ ተጨባጭ ለውጦች ማምጣቱን ገልጸዋል። የፓስፖርት እና የቪዛ አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎች የይለፍ ሰነዶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተደግፈው በጥራት እና በደህንነት እንዲመረት ተደርጓል ብለዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርቶች ታትመው ለዜጎች መሰራጨታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት መስጫ ማዕከላት ከነበሩበት 12 ወደ 23 በማሳደግ ተደራሽነቱ ማስፋፋት መቻሉን ጠቅሰው፥ በአየር እና በየብስ የድንበር መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች ከ7 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ መንገደኞች ቀልጣፋ አገልግሎት መሰጠቱን ጠቅሰዋል፡፡ የተቋሙን የሰው ኃይል አደረጃጀት እና ልማት በማሻሻል አገልግሎቱን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ለውጡን ለማረጋገጥ ወሳኝ እንደነበሩም ገልጸዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የአውሮፓ ሕብረት ከኢትዮጵያ ጋር በሁሉም ዘርፍ ያለውን ስትራቴጂክ ትብብር ለማስፋት ቁርጠኛ ነው
Jul 15, 2026 1377
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦የአውሮፓ ሕብረት ከኢትዮጵያ ጋር በሁሉም ዘርፍ ያለውን ስትራቴጂክ ትብብር ለማስፋት ቁርጠኛ መሆኑን የአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይና የደኅንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይና የአውሮፓ ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ካያ ካላስ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይና የደኅንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይና የአውሮፓ ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ካያ ካላስ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም በአውሮፓ ሕብረትና በአፍሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ላይ በመምከር፣ በጋራ ጥቅሞችና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ ተለዋውጠዋል። በተጨማሪም በቀጣናዊ እና ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ተመስርተው ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ይበልጥ ለማሳደግና ለማስፋፋት በሚያስችሉ መንገዶች ላይ መክረዋል። በተመሳሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ ከአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይና የደኅንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይና የአውሮፓ ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ካያ ካላስ ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም በኢትዮጵያና በአውሮፓ ሕብረት መካከል ያለውን የዘመናት ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የበለጠ ለማጠናከር፣ እንዲሁም በጋራ ጥቅም እና በአጋርነት ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። የኮሚሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንት ካያ ካላስ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአዲስ አበባ ጉብኝታቸው ሕብረቱ የኢትዮጵያንና የአፍሪካን ስትራቴጂክ አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችሉ ግብዓቶች የተገኙበት ነው። ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋር የነበራቸው ውይይት የኢትዮጵያንና የሕብረቱን አጋርነት ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር እንደሚያስችል ገልጸዋል። አያይዘውም፣ የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ የሚኖረውን የኢንቨስትመንት፣ የዲጂታል አስተዳደር፣ የታዳሽ ኃይል እና የሌሎች ዘርፎች ትብብር የበለጠ ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። የአውሮፓ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው ፍላጎት እያደገ መምጣቱም የንግድ ተቋማቱ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግና ሥራዎቻቸውን ለማስፋፋት ትልቅ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። ይህንን ዕድልም ለሁለቱም ወገኖች ተጠቃሚነት ለማዋል እንደሚሰራ ተገልጿል። የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና አዳዲስ የኢኮኖሚ ዕድሎችን ለመፍጠር እንደሚያግዙ ገልጸዋል። ኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት በዲጂታል አስተዳደር ዘርፍ ያላቸውን ትብብር እንደሚያጠናክሩ አመላክተዋል። በኢትዮጵያ ያለውን እምቅ የታዳሽ ኃይል ሀብት በመጥቀስ፤ ኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት በዘርፉ የቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ በመስራት ለጋራ ተጠቃሚነት ትልቅ ዕድል መፍጠር እንደሚችሉ አስረድተዋል። ሕብረቱ በአገሪቱ የጥሬ ዕቃዎች ላይ እሴት መጨመርን በመደገፍ የኢንዱስትሪ ልማት እንዲስፋፋ እንደሚያግዝ አረጋግጠዋል። ይህም ለሥራ ዕድል ፈጠራ መስፋፋት የሚኖረውን ወሳኝ ሚና ጠቁመዋል።      
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን የሚያጎለብቱ ተምሳሌታዊ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው
Jul 15, 2026 1041
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን የሚያጎለብቱ ተምሳሌታዊ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሚገኝ የፓርላማ መረጃ ደኅንነት ፎረም ተሳታፊ እና የምሥራቅና ደቡባዊ አፍሪካ አካውንታቢሊቲ ላብ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማክዶናልድ ሌዋኒካ ገለጹ። ኢትዮጵያ ለዘመናት የቆዩ አለመግባባቶችንና ልዩነቶችን ለመፍታት፣ እንዲሁም ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ሀገራዊ ምክክር እያካሄደች ትገኛለች። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ባለፉት አራት ዓመታት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እና በውጭ ሀገር ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በይፋ ተጀምሯል። የምሥራቅና ደቡባዊ አፍሪካ አካውንታቢሊቲ ላብ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማክዶናልድ ሌዋኒካ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ብሔራዊ መግባባትን የሚገነባ የዴሞክራሲ መንገድ ነው። አክለውም፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በመሠረታዊ ሀገራዊ ችግሮች ላይ ለመመካከርና መፍትሔ ለመስጠት በጉባኤው መሰባሰቡ ተምሳሌታዊ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ወደ መካሄድ መሸጋገሩ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን የሚያጎለብቱ ወሳኝ እርምጃዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት፣ የበርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውክልና ማግኘታቸው የዴሞክራሲ ባህልን ለማጎልበት ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል።    
በሲዳማ ክልል የህዝብና የአመራር አቅምን በማቀናጀት የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ማሳካት ተችሏል
Jul 15, 2026 957
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ):-በሲዳማ ክልል የህዝብና የአመራር አቅምን በማቀናጀት የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ማሳካት መቻሉን የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለጹ፡፡ ''ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት'' በሚል መሪ ቃል የክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ ሥራዎች አፈጻጻምን የሚገመግም መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል፡፡   የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ በወቅቱ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ የአመራርና የህዝብ አቅምን በማቀናጀት የግብርና ምርትና ምርታማነትን የማሳደግና ኢንዱስትሪውን በተገቢው በመምራት የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር ተችሏል። በተለይ የኑሮ ውድነትን ለማርገብ የግብርና ምርታማነትን ማሳደግን ጨምሮ ገበያ ተኮር ምርቶችን የማምረት ግብ ተይዞ ወደ ሥራ መገባቱን ጠቅሰው፣ በየደረጃው ያለው አመራር ተገቢውን ድጋፍ በማድረጉ ውጤት ተገኝቷል ብለዋል፡፡ ውሃ አጠር በሆኑ አካባቢዎች በጉድጓድ ውሃ ማልማት መጀመሩና መሬት ጾም እንዳያድር መደረጉም ምርታማነት እንዲጨምር ማድረጉን አያይዘው ገልጸዋል። የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳካትም ለክህሎት መር ስልጠና እንዲሁም የከተማና የገጠር የልማት አቅምችን ወደ ውጤት መቀየር ላይ በቅንጅት መሰራቱን አስረድተዋል። የገጠርና የከተማ ኮሪደር ልማቶች ኢኮኖሚና ማህበራዊ ፋይዳቸውን ለማጉላትም ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን ጠቅሰዋል።፡ መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ወደ ሥራ የገቡ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ቀደም ሲል ከአገልግሎት ጋር በተያያዘ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት አስችሏል ብለዋል፡፡ በተከናወኑ ሥራዎች በሁሉም ዘርፍ የተመዘገበው ውጤት አመራሩ ተናቦ በቁርጠኝነት ከሰራ ያቀዱትን ማሳካት እንደሚቻል ማሳያ ነው ብለዋል። በግምገማ መድረኩ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የበጀት ዓመቱ የፓርቲና የመንግስት ዕቅድ አፈጻፀም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
ኢትዮጵያን አሸናፊ እናድርግ- እናት ሙዶ አኮ
Jul 15, 2026 1028
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦ከደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ የካራ ማህበረሰብ ተወካይ እና የሰላም እናት ሙዶ አኮ በሀገራዊ የምክክር የመክፈቻ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያን አሸናፊ እናድርግ ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሂዷል።   በመክፈቻ ጉባኤው ከደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ የመጡት የካራ ማህበረሰብ ተወካይ እና የሰላም እናት ሙዶ አኮ፣ በዚሁ ወቅት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። እናት ሙዶ የኢትዮጵያ ሴቶች እና እናቶች ለዘመናት በታሪክ ሂደት ውስጥ ተሳትፏቸው የነበረው በደልን በመቀበል እና ሀዘንን በመጋራት ብቻ እንደነበር አስታውሰዋል። በዚህም እናቶች ለዘመናት በሰላም እጦት የደረሰባቸውን መከራ በንግግራቸው ጠቅሰዋል። ዛሬ ግን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምጻቸውን ለመስማት በመጥራቷ የኢትዮጵያ ሴቶችን ድምጽ በመወከል፣ ታሪካዊውን የምክክር መድረክ በክብር መቀላቀላቸውንም በደስታ ተናግረዋል። በዚህም በኢትዮጵያ ያላቸውን ተስፋ እና ሙሉ እምነት አንጸባርቀዋል። እናት ሙዶ አኮ፣ ሀገሪቱ ያሳለፈችው ፈታኝ ጊዜ የጋራ መግባባት በመጥፋቱ እንደሆነ በማሳየት ለነገ የምንተወው ተስፋ መሠረቱ የዛሬው መደማመጥ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የሁላችንም የጋራ መኖሪያ እንደሆነች ያነሱት እናት ሙዶ፣ በልባችን የያዝነውን የቀድሞ ቁጣ እና የቂም ቋጠሮ በመፍታት፣ ተመካካሪዎች በሙሉ ለሀገራዊ ለውጥ በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ማን ያሸንፋል ከሚል አስተሳሰብ በመውጣትም፣ ኢትዮጵያን አሸናፊ በሚያደርግ የጋራ ዓላማ ዙሪያ መሰለፍ እንደሚገባ በአጽንኦት ገልጸዋል። የምክክር መድረኩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና ብልፅግና ቁልፍ ምዕራፍ እንደሚሆንም ተናግረዋል። በመድረኩ ኢትዮጵያን አሸናፊ እናድርግ ያሉት እናት ሙዶ፥ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ የመገንባት ትልቅ አደራችንን እንወጣ ብለዋል።  
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የአፍሪካ ቀንድን ወደ ብሩህ ተስፋ የሚመራ አይነተኛ እርምጃ ነው -የኢጋድ ዋና ፀሐፊ
Jul 15, 2026 1201
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መላውን የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ወደ ብሩህ ተስፋ የሚመራ አይነተኛ እርምጃ መሆኑን የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ዛሬ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።   የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት በዓለም ታሪክ ውስጥ በግጭት የተገነባም ሆነ ያተረፈ ሀገር አለመኖሩን በመጥቀስ፣ የኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ልማት ሊረጋገጥ የሚችለው በሰላማዊ ውይይትና በመደማመጥ ብቻ እንደሆነ አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ማንነቷን የምትፈልግ አዲስ ሀገር ሳትሆን፣ ከጥንታዊና ጠንካራ ስልጣኔዎች አንዷ መሆኗን ጠቁመዋል። በታሪካችን፣ በባህላችንና በእምነታችን ውስጥ በርካታ ባህላዊ የእርቅ ስርዓቶች ስላሉ፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቁስል የምታክምበት ቁልፍ በእጇ ላይ መሆኑንና መፍትሔ ፍለጋ ወደ ውጭ ማማተር እንደማያስፈልጋት አጽንኦት ሰጥተዋል። በፖለቲካዊ ሕይወት ውስጥ በአስተዳደር፣ በሀብት ክፍፍልና በውክልና ዙሪያ የተለያዩ አመለካከቶች መኖራቸው ሙሉ በሙሉ ተፈጥሯዊና የተለመደ ነው ብለዋል። እነዚህን ልዩነቶች በኃይል ለመፍታት መሞከር ግን መሠረታዊ ስህተት መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እናቶች፣ አባቶች፣ ወጣቶችና ህጻናት ዛሬ የተወካዮቻቸውን መድረክ እየተመለከቱ ያሉት በጉጉትና በታላቅ ተስፋ እንደሆነ በማንሳት የግጭት አዙሪት በሀገሪቱ ማብቃት እንዳለበት ገልጸዋል። ልዩነቶችን በውይይትና በጋራ መከባበር መፍታት እንደምንችል ለራሳችንና ለዓለም የምናስመሰክርበት መድረክ ነው ብለዋል። የምክክር ጉባኤው ተሳታፊዎች ይህንን ታሪካዊ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም በአስተውሎት እንዲመካከሩ በመጠቆም፥ ኢጋድ በዚህ አስደናቂና ታሪካዊ የሰላም ጉዞ ውስጥ ከኢትዮጵያ ጎን በጽናት እንደሚቆም አረጋግጠዋል።  
ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን ለነገ እንድትሆን ሆና ልትገነባ ተሰባስባለች-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jul 15, 2026 1277
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን ለነገ እንድትሆን ሆና ልትገነባ ተሰባስባለች ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት ልሂቃን በሚፈጥሩት ግጭት ሕዝባችን ቢታመስም ባህላችን ግን ለምክክር ያደላ ነበር ብለዋል፡፡ ቤታችን፣ ሞሰባችን፣ አቀማመጣችን፣ ማብሰያችን፣ ወዘተ ክብ ናቸው።   ይሄውም ነገርን ሰብሰብ ብሎ በመመካከር ለመከወን እንዲያመች የተሠራ ነው። ክብ መነሻና መድረሻ የለውም። ሩቅና ቅርብ የለውም። ወጪና ገቢ የለውም። ሁሉንም በእኩልነት ያሳትፋል ሲሉ ገልፀዋል። ይሄንን የተረሳ ባህላችንን ወደ ሀገራዊ ምክክር አምጥተነዋል። ኢትዮጵያውያን ከአራቱም ማዕዘን መጥተው በጋራ ይመክራሉ። እሺ በጄ ያለ ሁሉ ዕድል ተሰጥቶታል። እነሆ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን ለነገ እንድትሆን ሆና ልትገነባ ተሰባስባለች ብለዋል ።   የሀገር ጸሎት ልብና ጆሮ ከእናንተ ጋራ ነው ሲሉም መልእክት አስተላልፈዋል።
ፖለቲካ
የአውሮፓ ሕብረት ከኢትዮጵያ ጋር በሁሉም ዘርፍ ያለውን ስትራቴጂክ ትብብር ለማስፋት ቁርጠኛ ነው
Jul 15, 2026 1377
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦የአውሮፓ ሕብረት ከኢትዮጵያ ጋር በሁሉም ዘርፍ ያለውን ስትራቴጂክ ትብብር ለማስፋት ቁርጠኛ መሆኑን የአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይና የደኅንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይና የአውሮፓ ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ካያ ካላስ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይና የደኅንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይና የአውሮፓ ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ካያ ካላስ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም በአውሮፓ ሕብረትና በአፍሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ላይ በመምከር፣ በጋራ ጥቅሞችና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ ተለዋውጠዋል። በተጨማሪም በቀጣናዊ እና ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ተመስርተው ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ይበልጥ ለማሳደግና ለማስፋፋት በሚያስችሉ መንገዶች ላይ መክረዋል። በተመሳሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ ከአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይና የደኅንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይና የአውሮፓ ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ካያ ካላስ ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም በኢትዮጵያና በአውሮፓ ሕብረት መካከል ያለውን የዘመናት ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የበለጠ ለማጠናከር፣ እንዲሁም በጋራ ጥቅም እና በአጋርነት ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። የኮሚሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንት ካያ ካላስ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአዲስ አበባ ጉብኝታቸው ሕብረቱ የኢትዮጵያንና የአፍሪካን ስትራቴጂክ አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችሉ ግብዓቶች የተገኙበት ነው። ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋር የነበራቸው ውይይት የኢትዮጵያንና የሕብረቱን አጋርነት ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር እንደሚያስችል ገልጸዋል። አያይዘውም፣ የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ የሚኖረውን የኢንቨስትመንት፣ የዲጂታል አስተዳደር፣ የታዳሽ ኃይል እና የሌሎች ዘርፎች ትብብር የበለጠ ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። የአውሮፓ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው ፍላጎት እያደገ መምጣቱም የንግድ ተቋማቱ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግና ሥራዎቻቸውን ለማስፋፋት ትልቅ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። ይህንን ዕድልም ለሁለቱም ወገኖች ተጠቃሚነት ለማዋል እንደሚሰራ ተገልጿል። የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና አዳዲስ የኢኮኖሚ ዕድሎችን ለመፍጠር እንደሚያግዙ ገልጸዋል። ኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት በዲጂታል አስተዳደር ዘርፍ ያላቸውን ትብብር እንደሚያጠናክሩ አመላክተዋል። በኢትዮጵያ ያለውን እምቅ የታዳሽ ኃይል ሀብት በመጥቀስ፤ ኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት በዘርፉ የቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ በመስራት ለጋራ ተጠቃሚነት ትልቅ ዕድል መፍጠር እንደሚችሉ አስረድተዋል። ሕብረቱ በአገሪቱ የጥሬ ዕቃዎች ላይ እሴት መጨመርን በመደገፍ የኢንዱስትሪ ልማት እንዲስፋፋ እንደሚያግዝ አረጋግጠዋል። ይህም ለሥራ ዕድል ፈጠራ መስፋፋት የሚኖረውን ወሳኝ ሚና ጠቁመዋል።      
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን የሚያጎለብቱ ተምሳሌታዊ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው
Jul 15, 2026 1041
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን የሚያጎለብቱ ተምሳሌታዊ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሚገኝ የፓርላማ መረጃ ደኅንነት ፎረም ተሳታፊ እና የምሥራቅና ደቡባዊ አፍሪካ አካውንታቢሊቲ ላብ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማክዶናልድ ሌዋኒካ ገለጹ። ኢትዮጵያ ለዘመናት የቆዩ አለመግባባቶችንና ልዩነቶችን ለመፍታት፣ እንዲሁም ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ሀገራዊ ምክክር እያካሄደች ትገኛለች። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ባለፉት አራት ዓመታት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እና በውጭ ሀገር ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በይፋ ተጀምሯል። የምሥራቅና ደቡባዊ አፍሪካ አካውንታቢሊቲ ላብ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማክዶናልድ ሌዋኒካ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ብሔራዊ መግባባትን የሚገነባ የዴሞክራሲ መንገድ ነው። አክለውም፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በመሠረታዊ ሀገራዊ ችግሮች ላይ ለመመካከርና መፍትሔ ለመስጠት በጉባኤው መሰባሰቡ ተምሳሌታዊ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ወደ መካሄድ መሸጋገሩ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን የሚያጎለብቱ ወሳኝ እርምጃዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት፣ የበርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውክልና ማግኘታቸው የዴሞክራሲ ባህልን ለማጎልበት ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል።    
በሲዳማ ክልል የህዝብና የአመራር አቅምን በማቀናጀት የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ማሳካት ተችሏል
Jul 15, 2026 957
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ):-በሲዳማ ክልል የህዝብና የአመራር አቅምን በማቀናጀት የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ማሳካት መቻሉን የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለጹ፡፡ ''ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት'' በሚል መሪ ቃል የክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ ሥራዎች አፈጻጻምን የሚገመግም መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል፡፡   የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ በወቅቱ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ የአመራርና የህዝብ አቅምን በማቀናጀት የግብርና ምርትና ምርታማነትን የማሳደግና ኢንዱስትሪውን በተገቢው በመምራት የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር ተችሏል። በተለይ የኑሮ ውድነትን ለማርገብ የግብርና ምርታማነትን ማሳደግን ጨምሮ ገበያ ተኮር ምርቶችን የማምረት ግብ ተይዞ ወደ ሥራ መገባቱን ጠቅሰው፣ በየደረጃው ያለው አመራር ተገቢውን ድጋፍ በማድረጉ ውጤት ተገኝቷል ብለዋል፡፡ ውሃ አጠር በሆኑ አካባቢዎች በጉድጓድ ውሃ ማልማት መጀመሩና መሬት ጾም እንዳያድር መደረጉም ምርታማነት እንዲጨምር ማድረጉን አያይዘው ገልጸዋል። የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳካትም ለክህሎት መር ስልጠና እንዲሁም የከተማና የገጠር የልማት አቅምችን ወደ ውጤት መቀየር ላይ በቅንጅት መሰራቱን አስረድተዋል። የገጠርና የከተማ ኮሪደር ልማቶች ኢኮኖሚና ማህበራዊ ፋይዳቸውን ለማጉላትም ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን ጠቅሰዋል።፡ መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ወደ ሥራ የገቡ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ቀደም ሲል ከአገልግሎት ጋር በተያያዘ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት አስችሏል ብለዋል፡፡ በተከናወኑ ሥራዎች በሁሉም ዘርፍ የተመዘገበው ውጤት አመራሩ ተናቦ በቁርጠኝነት ከሰራ ያቀዱትን ማሳካት እንደሚቻል ማሳያ ነው ብለዋል። በግምገማ መድረኩ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የበጀት ዓመቱ የፓርቲና የመንግስት ዕቅድ አፈጻፀም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
ኢትዮጵያን አሸናፊ እናድርግ- እናት ሙዶ አኮ
Jul 15, 2026 1028
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦ከደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ የካራ ማህበረሰብ ተወካይ እና የሰላም እናት ሙዶ አኮ በሀገራዊ የምክክር የመክፈቻ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያን አሸናፊ እናድርግ ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሂዷል።   በመክፈቻ ጉባኤው ከደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ የመጡት የካራ ማህበረሰብ ተወካይ እና የሰላም እናት ሙዶ አኮ፣ በዚሁ ወቅት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። እናት ሙዶ የኢትዮጵያ ሴቶች እና እናቶች ለዘመናት በታሪክ ሂደት ውስጥ ተሳትፏቸው የነበረው በደልን በመቀበል እና ሀዘንን በመጋራት ብቻ እንደነበር አስታውሰዋል። በዚህም እናቶች ለዘመናት በሰላም እጦት የደረሰባቸውን መከራ በንግግራቸው ጠቅሰዋል። ዛሬ ግን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምጻቸውን ለመስማት በመጥራቷ የኢትዮጵያ ሴቶችን ድምጽ በመወከል፣ ታሪካዊውን የምክክር መድረክ በክብር መቀላቀላቸውንም በደስታ ተናግረዋል። በዚህም በኢትዮጵያ ያላቸውን ተስፋ እና ሙሉ እምነት አንጸባርቀዋል። እናት ሙዶ አኮ፣ ሀገሪቱ ያሳለፈችው ፈታኝ ጊዜ የጋራ መግባባት በመጥፋቱ እንደሆነ በማሳየት ለነገ የምንተወው ተስፋ መሠረቱ የዛሬው መደማመጥ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የሁላችንም የጋራ መኖሪያ እንደሆነች ያነሱት እናት ሙዶ፣ በልባችን የያዝነውን የቀድሞ ቁጣ እና የቂም ቋጠሮ በመፍታት፣ ተመካካሪዎች በሙሉ ለሀገራዊ ለውጥ በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ማን ያሸንፋል ከሚል አስተሳሰብ በመውጣትም፣ ኢትዮጵያን አሸናፊ በሚያደርግ የጋራ ዓላማ ዙሪያ መሰለፍ እንደሚገባ በአጽንኦት ገልጸዋል። የምክክር መድረኩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና ብልፅግና ቁልፍ ምዕራፍ እንደሚሆንም ተናግረዋል። በመድረኩ ኢትዮጵያን አሸናፊ እናድርግ ያሉት እናት ሙዶ፥ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ የመገንባት ትልቅ አደራችንን እንወጣ ብለዋል።  
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የአፍሪካ ቀንድን ወደ ብሩህ ተስፋ የሚመራ አይነተኛ እርምጃ ነው -የኢጋድ ዋና ፀሐፊ
Jul 15, 2026 1201
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ መላውን የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ወደ ብሩህ ተስፋ የሚመራ አይነተኛ እርምጃ መሆኑን የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ዛሬ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።   የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት በዓለም ታሪክ ውስጥ በግጭት የተገነባም ሆነ ያተረፈ ሀገር አለመኖሩን በመጥቀስ፣ የኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ልማት ሊረጋገጥ የሚችለው በሰላማዊ ውይይትና በመደማመጥ ብቻ እንደሆነ አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ማንነቷን የምትፈልግ አዲስ ሀገር ሳትሆን፣ ከጥንታዊና ጠንካራ ስልጣኔዎች አንዷ መሆኗን ጠቁመዋል። በታሪካችን፣ በባህላችንና በእምነታችን ውስጥ በርካታ ባህላዊ የእርቅ ስርዓቶች ስላሉ፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቁስል የምታክምበት ቁልፍ በእጇ ላይ መሆኑንና መፍትሔ ፍለጋ ወደ ውጭ ማማተር እንደማያስፈልጋት አጽንኦት ሰጥተዋል። በፖለቲካዊ ሕይወት ውስጥ በአስተዳደር፣ በሀብት ክፍፍልና በውክልና ዙሪያ የተለያዩ አመለካከቶች መኖራቸው ሙሉ በሙሉ ተፈጥሯዊና የተለመደ ነው ብለዋል። እነዚህን ልዩነቶች በኃይል ለመፍታት መሞከር ግን መሠረታዊ ስህተት መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እናቶች፣ አባቶች፣ ወጣቶችና ህጻናት ዛሬ የተወካዮቻቸውን መድረክ እየተመለከቱ ያሉት በጉጉትና በታላቅ ተስፋ እንደሆነ በማንሳት የግጭት አዙሪት በሀገሪቱ ማብቃት እንዳለበት ገልጸዋል። ልዩነቶችን በውይይትና በጋራ መከባበር መፍታት እንደምንችል ለራሳችንና ለዓለም የምናስመሰክርበት መድረክ ነው ብለዋል። የምክክር ጉባኤው ተሳታፊዎች ይህንን ታሪካዊ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም በአስተውሎት እንዲመካከሩ በመጠቆም፥ ኢጋድ በዚህ አስደናቂና ታሪካዊ የሰላም ጉዞ ውስጥ ከኢትዮጵያ ጎን በጽናት እንደሚቆም አረጋግጠዋል።  
ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን ለነገ እንድትሆን ሆና ልትገነባ ተሰባስባለች-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jul 15, 2026 1277
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን ለነገ እንድትሆን ሆና ልትገነባ ተሰባስባለች ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት ልሂቃን በሚፈጥሩት ግጭት ሕዝባችን ቢታመስም ባህላችን ግን ለምክክር ያደላ ነበር ብለዋል፡፡ ቤታችን፣ ሞሰባችን፣ አቀማመጣችን፣ ማብሰያችን፣ ወዘተ ክብ ናቸው።   ይሄውም ነገርን ሰብሰብ ብሎ በመመካከር ለመከወን እንዲያመች የተሠራ ነው። ክብ መነሻና መድረሻ የለውም። ሩቅና ቅርብ የለውም። ወጪና ገቢ የለውም። ሁሉንም በእኩልነት ያሳትፋል ሲሉ ገልፀዋል። ይሄንን የተረሳ ባህላችንን ወደ ሀገራዊ ምክክር አምጥተነዋል። ኢትዮጵያውያን ከአራቱም ማዕዘን መጥተው በጋራ ይመክራሉ። እሺ በጄ ያለ ሁሉ ዕድል ተሰጥቶታል። እነሆ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን ለነገ እንድትሆን ሆና ልትገነባ ተሰባስባለች ብለዋል ።   የሀገር ጸሎት ልብና ጆሮ ከእናንተ ጋራ ነው ሲሉም መልእክት አስተላልፈዋል።
ማህበራዊ
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአፍሪካ ደረጃ በአርዓያነት የሚጠቀስ ተቋም ነው
Jul 16, 2026 58
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአፍሪካ ደረጃ በአርዓያነት የሚጠቀስ ተቋም መሆኑን የአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል፡፡ የአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ በዚሁ ጊዜ፣ ተቋሙ በአህጉር ደረጃ ሞዴል መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ ሰፊ የለውጥ ጉዞ በማድረግ በአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ከሚታመኑባቸው የልህቀት ማዕከላት አንዱ መሆን ችሏል ብለዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ ወረርሽኞችን አስቀድሞ በመከላከል እንዲሁም ሲከሰቱ በፍጥነት በመቆጣጠር ረገድ የገነባው አቅም ለሌሎች አፍሪካውያን አገራት ትልቅ አርአያ መሆኑን አድንቀዋል። በአፍሪካ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የነበራቸው አገራት በቁጥር 12 ብቻ የነበሩ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 40 ማደጋቸውን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ፣ ለዚህ ዕድገት የኢትዮጵያ ተሞክሮ ትልቅ ሚና እንደነበረው ተናግረዋል። አህጉሪቱ በቀጣይ የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት ያላቸውን አገራት ቁጥር ወደ 50 ለማድረስ ግብ የጣለች ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዚህ ሂደት ውስጥ እንደ ዋና ሞዴል እንደምታገለግል አስረድተዋል። በአፍሪካ ጠንካራ የላቦራቶሪ ትስስር መኖር የሕብረተሰብ ጤና ሥራዎችን ለመከወን ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ማዕከሉ ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር የላቦራቶሪ ትስስር መረብ ለመገንባት ሥራ መጀመሩን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያም የዚህ የሙከራ ትግበራ መነሻ ከሆኑት ቀዳሚ አገራት አንዷ መሆኗን ገልጸዋል። የአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በቅርበትና በተቀናጀ መልኩ ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያንም በኢንስቲትዩቱ ባስመዘገበው ውጤትና በደረሰበት የልህቀት ደረጃ ሊኮሩ እንደሚገባ ጠቅሰዋል፡፡    
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓትና የላብራቶሪ አቅም ገንብታለች- ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ
Jul 16, 2026 55
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓትና የላብራቶሪ አቅም የገነባች ሀገር መሆኗን በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ ገለፁ። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በተገኙበት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ ይገኛል።   በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ በዚሁ ወቅት፥ ኢንስቲትዩቱ ባለፈው አንድ ክፍለ ዘመን በሕብረተሰብ ጤና ዘርፍ ላስመዘገባቸው ታላላቅ ስኬቶች አድናቆታቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን በሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች አስተዳደር ረገድ የዓለም ጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል አድርጎ ለመሰየም የሚያስችል የድጋፍ ደብዳቤ በቅርቡ ለጤና ሚኒስቴር እንደሚላክም ይፋ አድርገዋል። በተጨማሪም የኢንስቲትዩቱ የአደጋ ጊዜ አስተዳደር ቡድን ዓለም አቀፍ የእውቅና ማረጋገጫ የማግኘት ሂደት የጀመረ ሲሆን ይህ ሂደት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያገኘ የአደጋ ጊዜ አስተዳደር ቡድን ያላት ሁለተኛዋ የአፍሪካ ሀገር ትሆናለች ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ የቅኝት፣የላብራቶሪ፣ ምርምር፣ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትና ምላሽ እንዲሁም በማስረጃ ላይ የተመሠረተ የፖሊሲ ቀረጻን በማቀናጀት የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓት መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ግንባር ቀደም እና ጠንካራ ከሆኑ የሕብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ሥርዓቶች አንዱን መገንባት ችላለች ብለዋል። በቅርቡ የተከሰተውን የማርበርግ ወረርሽኝ በመከላከል ረገድ ኢትዮጵያ ፈጣንና ውጤታማ ምላሽ በመስጠት ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ችላለች ሲሉ ጠቅስዋል። የኢንስቲትዩቱ የዳበረ ልምድና የባለሙያዎች ብቃት አሁን ላይ ከኢትዮጵያ አልፎ ለሌሎች ጎረቤት ሀገራት በቴክኒክ ትብብር፣ በላብራቶሪ አገልግሎትና በሕብረተሰብ ጤና አመራር ዘርፍ ከፍተኛ ድጋፍ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 11 ቀን 1947 የዓለም ጤና ድርጅት መስራች አባል በመሆን በይፋ የተቀላቀለች ሲሆን ባለፉት 79 ዓመታት ከድርጅቱ ጋር በመሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የጤና ሥርዓትን በመቅረጽ ረገድ ጉልህ ሚና ስትጫወት መቆየቷን አስታውሰዋል። ከሁሉም ስኬቶች ጀርባ ያለው የኢትዮጵያ ትልቁ ሀብት ሕዝቧና በኤፒዲሚዮሎጂ፣ በላብራቶሪ ሳይንስና በአደጋ ጊዜ አስተዳደር ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል ነው ሲሉ ተናግረዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፣ አዳዲስና ዳግም የሚቀሰቀሱ በሽታዎች፣ የጸረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች መላመድ እና ሰብአዊ ቀውሶች የወደፊቱን የጤና ገጽታ እየቀየሩት መሆኑን ጠቅሰዋል። እነዚህን ለመቋቋም እንደ ኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ያሉ ተቋማትን ማጠናከር፣ ጠንካራ አጋርነት መፍጠርና የማይበገሩ የጤና ሥርዓቶችን መገንባት የግድ ይላል ብለዋል። የዓለም ጤና ድርጅት ኢንስቲትዩቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፣ የዲጂታል ጤና ሥርዓትን ለማስፋፋትና ዓለም አቀፍ የጤና ደንቦችን ተግባራዊ ለማድረግ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና የብሔራዊ ደህንነት ዋነኛ መሰረት መሆኑን በጽኑ ያምናል-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ
Jul 16, 2026 101
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግስት የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና የብሔራዊ ደህንነት ዋነኛ መሰረት መሆኑን በጽኑ ያምናል ሲሉ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በተገኙበት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል። ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለዜጎች ጤንነትና ለሀገር ደህንነት ያለው ሚና ወሳኝ ነው፡፡ የኢንስቲትዩቱ የመቶ ዓመት ጉዞ ኢትዮጵያ ለዜጎቿ ጤና የምታደርገው ጥረትና የጤና ሥርዓት ግንባታ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። የሀገር ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ደህንነት ከህብረተሰብ ጤና ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳለው ጠቅሰው፥ የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ ጥንካሬ የወደፊት እርምጃዋ በዜጎቿ ጤና መጠበቅ ላይ የተመሠረተ ነው ብለዋል፡፡ በዚህ ሂደት የሕክምና ምርምር አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ፈታኝ የሆኑ ዓለም አቀፋዊ የጤና ቀውሶችን፣ ወረርሽኞችንና የተላላፊ በሽታዎችን በመከላከል ረገድ ያሳየው አፈጻጸም የሚደነቅ ነው ሲሉም ተናግረዋል። በተለይም እንደ ኮቪድ-19፣ ኤምፖክስ እና ማርበርግ ባሉ ወረርሽኞች ወቅት ኢንስቲትዩቱ ያሳየው ፈጣን ምላሽና ሳይንሳዊ አመራር ለሀገሪቱ ክብርን ያጎናጸፈ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማት፣የኢኮኖሚ ዕድገትና የብሔራዊ ደህንነት ዋነኛ መሠረት መሆኑን በጽኑ ያምናል ነው ያሉት ፕሬዝዳንት ታዬ። መንግሥት ጠንካራ ተቋማትን የሀገር ግንባታ መሠረት አድርጎ እንደሚመለከት በማስታወስ፣ ለኢንስቲትዩቱ የመሠረተ ልማትና የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል። ኢንስቲትዩቱ ለወደፊቱ ይበልጥ ውጤታማና ተወዳዳሪ እንዲሆን መንግሥት አመቺ የፖሊሲ መደላድልን እንደሚፈጥርም ተናግረዋል። ባለፉት ስኬቶች ላይ በመመሥረት የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን የመከላከልና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅምን ማዘመን እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተጨማሪም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የበሽታዎችን ስርጭት አስቀድሞ መተንበይ የሚያስችል ፈጣንና ዘመናዊ መረጃ አያያዝና ትንተና ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባም ጠቅሰዋል። የኢንስቲትዩቱ መቶኛ ዓመት የምስረታ በዓል ያለፈውን የሚዘክርበት፣ የአሁኑን የሚያመሰግኑበትና ለወደፊቱ የላቀ ዕቅድ የሚያቅዱበት መሆኑንም ገልጸዋል። የኢንስቲትዩቱ የፅናት፣ የእድሜና የህልውና ሚስጥር የሚቀዳው ከሰራተኞቹና ከተመራማሪዎቹ ጥንካሬ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ መንግሥት ለኢንስቲትዩቱ ተልዕኮ መሳካት ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በ100 ዓመታት ለዜጎች የጤና ጥበቃ ውጤታማ ዘመን የማይሽረው አሻራ አሳርፏል
Jul 16, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለፉት 100 አመታት ለዜጎች ጤና ጥበቃ ውጤታማነት ዘመን የማይሽረው የጥናትና ምርምር አሻራ ማሳረፉን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ገለጹ። ኢንስቲትዩት የ100ኛ በዓሉን ከዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያከብራል።   የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት፣ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል። በክብረ በዓሉ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ (ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባን ጨምሮ የአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት 100 ዓመታት ለኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ጥበቃና ደኅንነት ዘርፎች ውጤታማ ሳይንሳዊ የጥናትና ምርምር ተግባራትን በማከናወን፣ ዘመን የማይሽረው ታሪካዊ አሻራ አሳርፏል። ኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ቀድሞ በመለየትና ምርምር በማካሄድ፣ የተለያዩ ክትባቶችን በማምረት እንዲሁም ለጤና አደጋዎች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ረገድ ውጤታማ ሲሆን መቆየቱን ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ የጤና ፖሊሲና ስትራቴጂ ቀረጻ ላይ ሳይንሳዊ የጥናት ውጤቶችን እንደ ግብዓት በማቅረብ፣ የሚከሰቱ ወረርሽኞችን ቀድሞ በማወቅ፣ በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ጥራት ያለው የላብራቶሪ ምርመራ ሥርዓት በመዘርጋት እንዲሁም የሙያተኞችን አቅም በመገንባት ውጤታማ ተግባራትን እንዳከናወነ አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም ወረርሽኞችን አስቀድሞ የመተንበይና የመረጃ ፍሰትን የማዘመንና የማሳደግ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ኢንስቲትዩቱን በምሥራቅ አፍሪካ የሕዝብ ጤና ምርምርና ስልጠና ግንባር ቀደም ተቋም ለማድረግ ራዕይ ሰንቆ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ የ100ኛ ዓመት በዓሉን ከዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያከብራል።
ኢኮኖሚ
በክልሉ ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ ለልማትና ለመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል
Jul 16, 2026 44
ቡታጅራ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል። የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ ተግባቦት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ነው።   በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ የክልሉን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝብን የልማትና የመልካም እስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ፡፡ በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የዘርፉ አመራር ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ጠቅሰዋል፡፡ የገቢ አሰባሰብ ስራውን በልዩ ድጋፍና ክትትል በመምራት በዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በማረም በክልሉን ፈጣን እድገት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡   የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቀመሪያ ረሻድ በበኩላቸው ለክልሉ ህዝብ የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ገቢን በአግባቡ የመሰብሰብ ስራው በልዩ በትኩረት እየተመራ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ኃላፊዋ ገለጻ በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት 27 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 26 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰብ ተችሏል። ገቢው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ9 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ጠቅሰው ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ የተፈጠረው ግንዛቤ፣ የገቢ አሰባሰቡ ወጥ በመደረጉ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ መሰራቱ እና የድጋፍና ክትትል ስርዓት መጠናከሩ ለገቢው መጨመር አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በተጀመረው የ2019 በጀት ዓመት 35 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማሰባሰብ መታቀዱንና ይህንንም ለማሳካት የግብር ህጉን የማስከበር እና በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።        
ከንጋት ሐይቅ ከ10 ሺህ 700 ቶን በላይ የዓሳ ምርት ተገኝቷል
Jul 16, 2026 130
አሶሳ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- ከንጋት ሐይቅ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ10 ሺህ 700 ቶን በላይ የዓሳ ምርት መገኘቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ የተፈጠረው ግዙፍ ሰው ሰራሽ ሃይቅ (ንጋት ሃይቅ) የኤሌክትሪክ ሃይል ከማመንጨትና የቱሪስት መስህብ ከመሆን ባለፈ በዓሳ ምርት የስራ እድል መፍጠር ችሏል።   በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ላይ የተንጣለለው የንጋት ሃይቅ ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት ሲሆን በአካባቢው ልዩ ድባብ በመፍጠር ተመራጭ የመዝናኛ ስፍራ የሚሆን ነው። የንጋት ሃይቅ በተለይም ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልና አካባቢው ነዋሪዎች ተጨማሪ የኢኮኖሚ መሰረቶችን ይዞ የመጣ አቅም ሆኗል። የንጋት ሐይቅ የዓሣ ሃብት ልማት፣ የቱሪዝምና የውስጥ ለውስጥ የውሃ ትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲሁም በአካባቢው አዲስ የሥነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ሚዛን ለማስጠበቅ የሚያስችል ነው።   የክልሉ ግብርና ቢሮ የእንስሳት እና የዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ኢትቻ (ዶ/ር)፤ በንጋት ሐይቅ ዓሳ ማስገር ስራ 46 ማህበራት ተደራጅተው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከንጋት ሃይቅ ብቻ 1ዐ ሺህ 799 ቶን ዓሳ ማምረት መቻሉን ጠቅሰው በክልሉ የዓሳ ምርት እድገት ማሳያቱን ተናግረዋል። የተገኘው ምርት ከ2017 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በእጥፍ መጨመሩን ገልጸው በቀጣይም ተጨማሪ ማህበራት ወደ ስራ የሚገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።   በክልሉ ከንጋት ሀይቅ በተጨማሪ ከዳቡስ፣ ዲደሳ እና በለስ ወንዞች የዓሳ ምርት በብዛትና በጥራት መመረቱን አንስተው በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ከክልሉ የዓሳ ምርት ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎችም ከተሞች ለገበያ በማቅረብ ሁነኛ የገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ዶ/ር ብርሃኑ ገልጸዋል።   የንጋት ሐይቅ በተለይም በዓሳ ምርት ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ዓሳ በማስገርና ለገበያ በማቅረብ በሚያገኙት ገቢ ከራሳቸው አልፈው ለቤተሰባቸው ጭምር መትረፋቸውን ገልጸዋል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን በበጀት ዓመቱ ለ156 ሺህ ሰዎች ሥራ ተፈጥሯል
Jul 16, 2026 117
ጊምቢ፣ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ወለጋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት አመት ለ156 ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩን የዞኑ ሥራ ፈጠራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡ የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ደረጀ ጉድና ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በበጀት አመቱ ስራ አጥ ወገኖችን በማህበር በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል። በዞኑ በ2018 በጀት ዓመት ለ108 ሺህ ስራ አጥ ወገኖች የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ አፈፃሙን ከፍ በማድረግ ለ156 ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል ታጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል ብለዋል፡ በዞኑ የስራ አጥነት ችግር ለማቃለል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት የተከናወኑ ተግባራት አፈፃፀሙን ለማሳደግ እንዳስቻሉ ነው የተናገሩት። የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ወገኖች በግብርና፣ በንግድ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በእንስሳት ልማት፣በውበት ስራ እና በሌሎች ዘርፎች መሰማራታቸውን ነው የገለጹት። የስራ እድል ለተመቻቸላቸው ዜጎች ከ1 ቢሊዮን ብር ብድር እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በተሰማሩበት መስክ ዉጤታማ እንዲሆኑም የድጋፍና የክትትል ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ከስራ እድሉ ተጠቃሚዎች መካከል መፊዛ አብዲ ከሌሎች ጓደኞቿ ጋር በመሆን ዝሪያቸው የተሻሻሉ በጎችን በማድለብ ስራ ላይ መሰማራታቸውን ነው የምትናገረው። በተሰማሩበት መስክ የተሰጣቸው ሥልጠና፣ ድጋፍ አና ክትትልም ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያደርግ በመሆኑ የተሻለ ስኬት ለማስመዝገብ እየሰሩ መሆኑን ነው የገለፀችው።   በማኅበር ተደራጅተው የመሥሪያ ቦታና የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ በመሆን በዶሮ እርባታ ስራ ላይ መሰማራታቸውን የገለፀው ወጣት እዮብ ቶለሳ በዘርፉ ውጤታማ ስራዎችን እየሰራን ነው ብሏል። በተለይም ከቅርብ አመታት ወዲህ በመንግስት ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ የልማት ኢንሼቲቮች ወጣቱ የስራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን አመልክቷል።
በክልሉ ከተሞች መኖሪያ ቤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመገንባት የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት ይደረጋል
Jul 16, 2026 97
ጎንደር፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በከተሞች መኖሪያ ቤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመገንባት የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የተቀናጀ ጥረት የሚደረግ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ገለጸ። በክልሉ በተለይም በከተሞች የሚስተዋለውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለማቃለል የሚያስችል የተቀናጀ አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።   በዚህ የልማት ጥረት ውስጥ የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በጡብ ማምረት ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ ስልጠና በጎንደር ከተማ እየተሰጠ ይገኛል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አማካሪ አቶ ሽቤ ክንዴ፤ ኮሌጆቹ ቴክኖሎጅን የመቅዳት፣ የማላመድና የመፍጠር አቅማቸውን በመጠቀም የቤት ግንባታ ፕሮጀክት እቅዱ እንዲሳካ መስራት አለባቸው ብለዋል። በዘመናዊ መንገድ ጡብ በማምረት በከተሞች ደረጃቸውን የጠበቁ፣ ውብና ማራኪ ቤቶችን መገንባት አለብን ያሉት አቶ ሽቤ፤ ለዜህም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ከፍተኛ ሚና እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የዚህ ስልጠና ዋነኛ ዓላማም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ለእቅዱ መሳካት የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ነው ብለዋል። የስልጠናው ተሳታፊዎችም ለልማት ፕሮጀክቱ ስኬት የበኩላቸውን ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፤ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶችን ለመገንባት እቅድ መያዙን መግለፃቸው ይታወቃል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አገልግሎቱ የአሰራር ሥርዓቱን በማዘመን ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል
Jul 16, 2026 154
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዘመኑን የሚመጥን የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋፋት፣ የአሰራር ሥርዓቱን በማዘመን እና ምቹ የስራ ከባቢን በመፍጠር የተገልጋዩን እርካታ የሚያሳድጉ ተጨባጭ ለውጦች ማምጣቱን ዋና ዳይሬክተሯ ሰላማዊት ዳዊት ገለጹ፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት፤ ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።   በመግለጫቸውም፥ተቋሙ ዘመኑን የሚመጥን የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋፋት፣ የአሰራር ሥርዓቱን በማዘመን እና ምቹ የስራ ከባቢን በመፍጠር የተገልጋዩን እርካታ የሚያሳድጉ ተጨባጭ ለውጦች ማምጣቱን ገልጸዋል። የፓስፖርት እና የቪዛ አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎች የይለፍ ሰነዶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተደግፈው በጥራት እና በደህንነት እንዲመረት ተደርጓል ብለዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርቶች ታትመው ለዜጎች መሰራጨታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት መስጫ ማዕከላት ከነበሩበት 12 ወደ 23 በማሳደግ ተደራሽነቱ ማስፋፋት መቻሉን ጠቅሰው፥ በአየር እና በየብስ የድንበር መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች ከ7 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ መንገደኞች ቀልጣፋ አገልግሎት መሰጠቱን ጠቅሰዋል፡፡ የተቋሙን የሰው ኃይል አደረጃጀት እና ልማት በማሻሻል አገልግሎቱን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ለውጡን ለማረጋገጥ ወሳኝ እንደነበሩም ገልጸዋል።
የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እየፈታ ነው
Jul 14, 2026 836
አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፡-የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መንግስታዊ አሰራርን በማቀናጀት ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እንደፈታላቸው ተገልጋዮች ገለጹ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ክላስተር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች እንዳሉት የማዕከሉ ቀልጣፋ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት አስችሏል፡፡   ከተገልጋዮቹ መካከል ፓስፖርት ለማውጣት በማዕከሉ የተገኙት አቶ ገብረእግዚአብሔር ሃይለስላሴ በማዕከሉ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመጨረስ አስችሏቸዋል። ይህም ቀደም ሲል በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ሲስተዋል በነበረ መጓተት ይፈጠር የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር መፍታት ችሏል ብለዋል። የማዕከሉ ሠራተኞች አክብሮት የተሞላበት አገልግሎት እንደሰጧቸው ገልጸው፣ በማዕከሉ የተለያዩ አገልግሎቶች መስጠታቸው ጊዜ፣ ወጪና እንግልትን አስቀርቶልናል ብለዋል። አገልግሎቱ በዲጂታል ሥርአት የታገዘ መሆኑ ቀልጣፋና ከሙስና የጸዳ አገልግሎት በፍትሀዊነት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።   ዜጎችን ለምሬት ይዳርግ የነበረውን የመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥ ያስተካከለው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ ዘላለም አሸናፊ ናቸው። የአገልግሎቱ ቀልጣፋና ውጤታማነት መንግስት አሰራሩን በማዘመን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። እሳቸውም የንግድ ፈቃዳቸውን ለማውጣት በመጡበት ወቅት ወደ ተለያዩ ተቋማት መሄድ ሳያስፈልጋቸው አገልግሎቶቹን ከመሶብ አገልግሎት ብቻ በተሟላ ሁኔታ ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ክላስተር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስተባባሪ አቶ ይበቃል አሰፋ በበኩላቸው በማዕከሉ አምስት የክልልና አራት የፈደራል ተቋማት 32 አይነት አገልግሎቶች በዲጅታል ታግዘው እየተሰጡ መሆኑን አስረድተዋል። ይህም ዜጎች ፍትሃዊ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ከእንግልት፣ ከእጅ መንሻና መሰል ችግሮች እንደታደጋቸው ገልጸዋል። አሰራሩ መዘመኑ ስራን ከማቀላጠፍ ባለፈ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን በዘላቄታው ለመፍታት አስችሏል ብለዋል።  
ዲጂታል የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ ትክክለኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲዎችን ለመቅረጽ ወሳኝ ነው
Jul 13, 2026 753
ድሬዳዋ፣ሐምሌ6/2018 (ኢዜአ)፡-ዲጂታል የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባን ውጤታማ ማድረግ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲዎችን በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርቶ ለመቅረጽ ወሳኝ መሆኑን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ገለጸ። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አገልግሎት ጋር በመሆን የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ዲጂታል ሲስተምን በድሬዳዋ አስጀምረዋል።   በማስጀመሪያ ሥነስርአቱ ላይ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት እንደተናገሩት፤ ዲጂታል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ሥርአትን በተቀናጀ መልኩ መስጠት ተደራሽነትን ያሰፋል። ዲጂታል የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባን ውጤታማ ማድረግ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲዎችን በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርቶ ለመቅረጽ ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል። በተጨማሪም በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ዕቅዶችን አውጥቶ አፈጻጸማቸውን ለመከታተል ጉልህ ጠቀሜታ እንዳለውም አንስተዋል። የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ዲጂታል አገልግሎት ለስታስቲክስ መረጃዎች ትንተና እንዲሁም ለፖሊሲ አውጪዎች ትክክለኛ መረጃ ለመስጠት ወሳኝ መሆኑንም ነው ዋና ዳይሬክተሯ ያመለከቱት።   የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው በድሬዳዋና አዲስ አበባ አገልግሎቱ የተጀመረው የሲቪልና ቤተሰብ ዲጂታል አገልግሎት "የዲጂታል 2030" ትግበራ አካል መሆኑን አንስተዋል። ተግባሩ ቀልጣፋ አገልግሎትን ዕውን በማድረግ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በላቀ ውጤት ለመፍታት እንደሚያስችልም ገልጸዋል። ዲጂታል አገልግሎቱ የልደት፣ የጋብቻ፣ የሞት መረጃዎችን በቴክኖሎጂ በመቀመር ለሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ መሳካት ለማዋል በትኩረት ሲሰራ መቆየቱንም አንስተዋል።   የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በበኩላቸው ዛሬ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ በድሬዳዋ ወደ ተግባር የተሻገረው ዲጂታል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት፣ ለድሬዳዋ ሁለንተናዊ ብልፅግና ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። የተጀመረውን ዲጂታል አገልግሎት ከመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጋር ተሳስሮ የላቀ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለህዝብ ለመስጠት ያስችላል ብለዋል። በሥነስርዓቱ ላይ የፌደራል እና የድሬዳዋ አስተዳደር ባለስልጣናት፣ የተቋማት አመራሮች፣ የኃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ተሳትፈዋል።  
የአፍሪካን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የሚያሳልጥ የዲጂታል አቅም መገንባት ያስፈልጋል 
Jul 13, 2026 819
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የሚያሳልጥ የዲጂታል ሥርዓት መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ገለጸ። የአፍሪካ የትምህርት ፈጠራ ኤክስፖ 2026 በአፍሪካ ህብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ነው። ''የትምህርት ዲጂታል ሽግግርና የፈጠራ መፍትሔዎችን ማሳደግ'' በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ኤክስፖ የፈጠራ ባለቤቶች፣ የጥናትና ምርምር ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያን ክምቢና በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በአፍሪካ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ብቁ የሰው ሃይል መገንባት ያስፈልጋል። ለዚህም በአፍሪካ ሕብረት በተገባው የፖለቲካ ቁርጠኝነት መሰረት አፍሪካዊያን በተለወጠ ዓለም ውስጥ የትውልዱን ዕውቀትና ክህሎት ለማዳበር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካን ትምህርት ወደ ዲጂታል ማሸጋገር ወቅታዊ እና የሀገራትን ትኩረት የሚፈልግ ነው ብለዋል። በአፍሪካ አካታች የዲጂታል ትምህርት ስርአት በመዘርጋት የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ፣ የዲጂታል የትምህርት ግብዓቶችን ማሟላት ላይም ይበልጥ መስራት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። ትምህርትን በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተቃኘ ማድረግ እና የአስተማሪዎችን የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደግ ትምህርትን ለማሸጋገር ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም አክለዋል። የጥናትና ምርምር ተቋማትን አቅም ማሳደግም የሀገራት የትኩረት ማዕከል ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ ህብረትም በአህጉሪቱ ትምህርትን ለማዘመን የሚሰሩ ተግባራትን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።
ስፖርት
አርጀንቲና እንግሊዝን በመርታት ለፍጻሜ አለፈች
Jul 15, 2026 889
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር አርጀንቲና ከመመራት ተነስታ እንግሊዝን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ማምሻውን በአትላንታ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የ25 ዓመቱ የክንፍ መስመር ተጫዋች አንቶኒ ጎርደን በ55ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ጎል እንግሊዝን መሪ አድርጓል። ሞርጋን ሮጀርስ ኳሷን አመቻችቶ አቀብሏል። አርጀንቲና ከግቡ መቆጠር በኋላ ተጭና ተጫውታለች። ኤንዞ ፈርናንዴዝ በ85ኛው ደቂቃ በግሩም ሁኔታ ከመረብ ላይ ያሳረፈው ጎል አርጀንቲናን አቻ አድርጓል። ላውታሮ ማርቲኔዝ በ92ኛው ደቂቃ የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። እንግሊዝ መሪነቷን ማስጠበቅ አልቻለችም። ጨዋታው ጉልበት እና ኃይል የተቀላቀለበት ነበር። በርካታ ጥፋቶችም ተሰርተዋል። ሊዮኔል ሜሲ ለ12ኛ ጊዜ በዓለም ዋንጫ ለግብ የሚሆን ኳስ በማቀበል አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ስምንት ጎሎችን አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ አርጀንቲና ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ አልፋለች። የወቅቱ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ አርጀንቲና ለስድስተኛ ጊዜ ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ደርሰዋል። አርጀንቲና በፍጻሜው ከስፔን ጋር ትገናኛለች። እንግሊዝ ለሁለተኛ ጊዜ ለዓለም ዋንጫ የማለፍ ህልሟ አልተሳካም። እንግሊዝ ከፈረንሳይ ሶስተኛ ደረጃን ለማግኘት ቅዳሜ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ይጫወታሉ። ስፔን ከአርጀንቲና ዋንጫውን ለማንሳት እሁድ ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም ይፋለማሉ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስፖርት መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ብቁ ዜጋ የማፍራት ሥራ ተጠናክሯል 
Jul 15, 2026 351
ወልቂጤ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በክልሉ የስፖርት መሰረተ ልማትን በማስፋፋት በአካልና በአዕምሮ የዳበረ ዜጋን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ገለጸ። በወልቂጤ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተገኙበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርሃ ግብር ተካሄዷል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ እንደገለጹት፤ በክልሉ የስፖርት ልማትን በማስፋፋት በአካልና በአዕምሮ የዳበረ ጤናማና ብቁ ዜጋ ለማፍራት እየተሰራ ነው።   ለዚህም በየአካባቢው የስፖርት ማዘወተሪያዎችን ከማስፋፋት ባለፈ ስፖርትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተው፣ የዛሬው ስፖርታዊ እንቅስቃሴም የዚሁ አካል ነው ብለዋል። በተለይ ወጣቶች ስፖርትን በማዘወተር ያላቸውን ተሰጥኦ እንዲያጎለብቱ መሰራቱን ገልጸዋል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴው የእርስ በርስ ትስስርንም ያጠናክራል ብለዋል። የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር በበኩላቸው፤ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ከጤና ጥቅሙ ባለፈ የዜጎችን የአብሮነት እሴት የሚያጎለብትና በራሱ የሚተማመን ትውልድ ለመቅረጽ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።   ለዚህም ከተማዋ በብስክሌት፣ በቅርጫት ኳስ፣ በእግር ኳስ ጠንካራ ስፖርተኞች ለማፍራት የሚያስችል የስፖርት መሰረተ ልማቶችን እየገነባች መሆኑን አክለዋል። ይህም ለከተማዋ ኢኮኖሚና የስፖርት ቱሪዝም መነቃቃት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከተሳታፊዎች መካከል ኢንስፔክተር አብድልሰመድ መሃመድ፤ በከተማዋ የስፖርት ልማቱን የሚያቀላጥፉ መሰረተ ልማቶች መከናወናቸው የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል።   የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርሀግብሩ በስፖርት ጤናማና ብቁ ዜጋ ለመገንባት ለሚደረገው ጥረት አጋዥ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ ካሚል ጀማል ናቸው።   መርሀግብሩ የእርስ በርስ ግንኙነትን በማጠናከር የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን በጋራ ለማከናወን ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸውም ጠቅሰዋል።
ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ማን ያልፋል? እንግሊዝ ወይስ አርጀንቲና? ተጠባቂው ፍልሚያ!
Jul 15, 2026 494
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ሁለተኛ የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር እንግሊዝ ከአርጀንቲና ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ጨዋታው ምሽት አራት ሰዓት ላይ በአትላንታ ስታዲየም ይካሄዳል። እንግሊዝ በሩብ ፍጻሜው ኖርዌይን 2 ለ 1 በማሸነፍ የመጨረሻ አራት ውስጥ ገብታለች። ሶስቱ አናብስቶች ለግማሽ ፍጻሜ ሲያልፉ የአሁኑ ለአራተኛ ጊዜ ነው። ተጋጣሚዋ አርጀንቲና ስዊዘርላንድን 3 ለ 1 በመርታት ለግማሽ ፍጻሜ አልፋለች። የወቅቱ የዓለም ሻምፒዮን አርጀንቲና አራት ውስጥ ስትገባ ለሰባተኛ ጊዜ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የደቡብ አሜሪካዋ ሀገር ከዚህ ቀደም ያደረጋቻቸውን ስድስት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች በሙሉ በማሸነፍ ስኬታማ ክብረ ወሰን አላት። እንግሊዝ በበኩሏ ከሶስት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች መካከል ያሸነፈችው አንዱን ብቻ ነው። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ከዚህ ቀደም አምስት ጊዜ ተገናኝተዋል። እ.አ.አ በ1962 በቺሊ በተካሄደው ሰባተኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በምድብ አራት ተገናኝተው እንግሊዝ አርጀንቲናን 3 ለ 1 አሸንፋለች። እንግሊዝ እ.አ.አ በ1966 ባዘጋጀችው ስምንተኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ላይ ተገናኝተው አዘጋጇ ሀገር 1 ለ 0 ያሸነፈች ሲሆን እስከ መጨረሻው በመጓዝ ምዕራብ ጀርመን (በወቅቱ በነበረው ስያሜዋ) በማሸነፍ ዋንጫውን አንስታለች። በሀገራቱ የዓለም ዋንጫ ግንኙነት ውስጥ ሁሌም የሚታወሰው ጨዋታ እ.አ.አ በሜክሲኮ አዘጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በሩብ ፍጻሜው የተገናኙበት መርሐ ግብር ነው። አርጀንቲና እንግሊዝን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜ አልፋለች። ዲያጎ ማራዶና ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በወቅቱ ማራዶና በእጁ ያስቆጠራት አወዛጋቢ ጎል “ የፈጣሪ እጅ” (Hand of God) እየተባለች ትጠራለች። አርጀንቲና ፍጻሜ በመድረስ ምዕራብ ጀርመንን (በወቅቱ የነበረው አጠራሯ) በማሸነፍ ዋንጫውን ለሁለተኛ ጊዜ አንስታለች። ፈረንሳይ እ.አ.አ በ1998 ባዘጋጀችው 16ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በሩብ ፍጻሜው መርሐ ግብር 16 ውስጥ ተገናኝተው በጨዋታ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቆ አርጀንቲና በመለያ ምት 4 ለ 3 በማሸነፍ ለሩብ ፍጻሜው አልፋለች። ቡድኖቹ ለመጨረሻ ጊዜ በውድድሩ ላይ የተገናኙት ኮሪያ ሪፐብሊክ እና ጃፓን እ.አ.አ በ2002 ባዘጋጁት 17ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ላይ ነበር። በምድብ ስድስት ባደረጉት ጨዋታ እንግሊዝ በዴቪድ ቤካም የፍጹም ቅጣት ምት ጎል 1 ለ 0 አሸንፋለች። ሁለቱ ሀገራት ከ24 ዓመታት በኋላ በመድረኩ ለፍጻሜ ለማለፍ የሚያደርጉት ጨዋታ ትኩረትን ስቧል። ብሔራዊ ቡድኖቹ በውድድር እና ወዳጅነት ጨዋታዎች በአጠቃላይ 14 ጊዜ ተገናኝተው እንግሊዝ ስድስት ጊዜ ድል ሲቀናት አርጀንቲና በሶስቱ ጨዋታዎች አሸንፋለች። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች ላይ አቻ ተለያይተዋል። በ14ቱ ጨዋታዎች ላይ እንግሊዝ 21 ጎሎችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ አርጀንቲና 15 ግቦችን አስቆጥራለች። እንግሊዝ የዓለም ዋንጫን አንድ ጊዜ ስታነሳ አርጀንቲና የሶስት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ናት። በዘንድሮው ዓለም ዋንጫ በተመሳሳይ ስድስት ግቦችን ያስቆጠሩት ሃሪ ኬን እና ጁድ ቤሊንግሃም በዛሬው ጨዋታ የሚጠበቁ ተጫዋቾች ናቸው። የ39 ዓመቱ ሊዮኔል ሜሲ በጨዋታው ትኩረትን ያገኘ ተጫዋች ነው። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ስምንት ግቦችን በማስቆጠር ለኮከብ ግብ አግቢነት እየተፎካከረ ይገኛል። ሜሲ በአጠቃላይ በዓለም ዋንጫ 21 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። የአማካይ ተጫዋቹ ሮድሪጎ ዲ ፖል ከአርጀንቲና በኩል በጨዋታው ልዩነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። አርጀንቲና በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ በርካታ ግቦችን (17) ያስቆጠረች ሀገር ናት። እንግሊዝ ለሁለተኛ ጊዜ፣ አርጀንቲና ለሰባተኛ ጊዜ ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ለማለፍ ይፋለማሉ። ጨዋታው ጠንካራ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል። አሸናፊው ሀገር ከስፔን ጋር በፍጻሜው ይገናኛል። ትናንት በተደረገው የመጀመሪያ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ስፔን ፈረንሳይን 2 ለ 0 በመርታት የፍጻሜው ተፋላሚ ሆናለች።
ስፔን ፈረንሳይን በመርታት ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ አለፈች
Jul 14, 2026 670
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ተጠባቂ የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን ፈረንሳይን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በዳላስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማይክል ኦያርዛባል በ22ኛው ደቂቃ የመጀመሪያውን ጎል በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል። ፍጹም ቅጣት ምቱ የተገኘው የፈረንሳዩ ተከላካይ ሉካ ዲኝ በላሚን ያማል ላይ በሰራው ጥፋት ነው። የ29 ዓመቱ አጥቂ ኦያርዛባል በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት አምስት አድርሷል። ፔድሮ ፖሮ በ58ኛው ደቂቃ ሁለተኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው ስፔን በኳስ ቁጥጥር እና የግብ እድሎችን በመፍጠር አንጻራዊ ብልጫ ነበራት። የፈረንሳይ የአጥቂ መስመር ክፍል በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያሳየውን አስፈሪነት በዛሬው ጨዋታ መድገም አልቻለም። በአጠቃላይ ፈረንሳይ በሚጠበቀው የብቃት ደረጃ ላይ አልነበረችም። የ25 ዓመቱ የፈረንሳይ ተከላካይ ዊሊያም ሳሊባ በ30ኛው ደቂቃ በጉዳት ምክንያት ተቀይሮ ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ ስፔን ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ አልፋለች። ስፔን ከ19ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ የፍጻሜውን ትኬት ቆርጣለች። የአንድ ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ስፔን በዘንድሮው ውድድር ምንም ሽንፈት ያላስተናገደች ሀገር ሆናለች። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫም የተቆጠረባት አንድ ግብ ብቻ ነው። ስፔን በፍጻሜው ከእንግሊዝ እና አርጀንቲና አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ለዋንጫው የተጠበቀችው ፈረንሳይ ለፍጻሜ መብቃት አልቻለችም። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ሽንፈቷን አስተናግዳለች። የሁለት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ፈረንሳይ ለአምስተኛ ጊዜ ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ የማለፍ ህልሟ ሳይሳካ ቀርቷል። ፈረንሳይ ከእንግሊዝ እና አርጀንቲና ተሸናፊ ጋር ሶስተኛ ደረጃን ለማግኘት ትጫወታለች። በዓለም ዋንጫው ስምንት ጎሎችን ያስቆጠረው ኪሊያን እምባፔ ለሁለት ተከታታይ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ የማለፍ ህልሙ ሳይሳካ ቀርቷል። እምባፔ አሁንም ለከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱ መፎካከሩን ይቀጥላል። የ27 ዓመቱ አጥቂ 21ኛ የዓለም ዋንጫ በማድረግ ለፈረንሳይ በውድድሩ ላይ በርካታ ጨዋታዎችን ያደረገ ተጫዋች ሆኗል። በነዚህ ጨዋታዎች ላይ 20 ግቦችን አስቆጥሯል። ሁለተኛው የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር ነገ በእንግሊዝ እና አርጀንቲና መካከል ይደረጋል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ ለአረንጓዴ ልማት ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር አሳይታለች
Jul 16, 2026 87
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ ለአረንጓዴ ልማት ያላትን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ማሳየቷን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ፀጋ ገለጹ። በኢትዮጵያ የአረንጓዴ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ማጠናከር ላይ ለተቀረጸው የምርምር ፕሮጀክት የተዘጋጀ የማስጀመሪያ አውደ ጥናት እየተካሄደ ይገኛል። በአውደ ጥናቱ መክፈቻ ላይ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ፀጋ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ ለአረንጓዴ ልማት ያላትን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር አሳይታለች። ይህም በታዳሽ ኃይል መስፋፋት፣ በዘላቂ ግብርና እና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ በሆኑ የኢንዱስትሪ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በግልጽ ይንጸባረቃል ብለዋል። አረንጓዴ ኢኮኖሚን መገንባት የመንግሥትን ጥረት ብቻ ሳይሆን የሁሉንም አካላት ንቁ ተሳትፎ እንደሚጠይቅም አንስተዋል። በተለይም አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ማሳተፍ ወሳኝና አማራጭ የሌለው ተግባር መሆኑን ገልጸው፤ እነዚህ ኢንተርፕራይዞች ለኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለእሴት ሰንሰለት ዕድገት፣ ለሀገር ውስጥ ምርት እንዲሁም ለኢኮኖሚ ብዝኃነት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አስገንዝበዋል። በርካታ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ወደ አረንጓዴ ልማት በሚያደርጉት ጉዞ ላይ ፈተናዎች እየገጠሟቸው እንደሚገኝም ጠቁመዋል። ዛሬ ውይይት የሚደረግበት ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የሚገኙ የአረንጓዴ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን በጥናትና ምርምር በመገምገም፣ በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሠረቱ ምክረ ሐሳቦችን እንደሚያቀርብ አስታውቀዋል። የጥናቱ ዋና ዓላማ የኢንተርፕራይዞቹን የአረንጓዴ ሽግግር ወቅታዊ ሁኔታ፣ ዕድሎችና ፈተናዎች በግልጽ ማሳየት መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ለአረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት የሚያስፈልጉ የፖሊሲ፣ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የቴክኒክ ድጋፍ ማዕቀፎችን እንደሚለይም ጠቁመዋል። ለኢንተርፕራይዞች ዕድገትና ተወዳዳሪነት የሚበጅ ምቹ ምህዳር ለመፍጠር፣ የእያንዳንዱ ባለድርሻ አካል የሥራ ድርሻና አስተዋፅኦ ምን መሆን እንዳለበት በጥናቱ በጥልቀት እንደሚፈተሽም አብራርተዋል።  
የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖዎችን ለመቋቋም የተገቡ ቃሎች ወደ ተጨባጭ ተግባር መቀየር አለባቸው
Jul 15, 2026 1144
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 8/2018(ኢዜአ) ፦ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትላቸውን አሉታዊ ተፅዕኖዎች ለመቋቋም የተገቡ ቃሎችን ወደ ተጨባጭ ተግባር መቀየር አስፈላጊ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቴዎስ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኮፕ 32 ፕሬዚዳንት ዶክተር ጌዲዎን ጢሞቴዎስ ዛሬ ከኮፕ 21 ፕሬዚዳንት ከሆኑት ሎረን ፋቢየስ ጋር ተወያይተዋል። ‎ ‎በውይይቱም ሎረን ፋቢየስ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ ታላቅ ስኬት የተመዘገበበትን የፓሪስ ስምምነት በማጽደቅ የተጠናቀቀውን ኮፕ 21ን የመሩበትን ልምድ አካፍለዋል። ‎በተጨማሪም ለኮፕ 32 በሚደረጉ ዝግጅቶች እንዲሁም ስኬታማ የኮፕ 32 ጉባኤን ለማካሄድ አስተዋጽኦ ሊኖራቸው በሚችሉ ጉዳዮችና ካለፉት የኮፕ ጉባኤዎች በተገኙ ትምህርቶችና ግንዛቤዎች ላይ የሁለቱ መሪዎች ውይይት ትኩረት አድርጓል። ‎ ‎የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) የፓሪሱ ስምምነት ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት እርምጃዎች ያለውን ዘላቂ ጠቀሜታ ገልጸው፣ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትላቸውን አሉታዊ ተፅዕኖዎች ለመቋቋም የተገቡ ቃሎችን ወደ ተጨባጭ ተግባር የመቀየርን አስፈላጊነት አፅንዖት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ላይ እምነትን የሚያጠናክር፣ ግልጽ፣ አካታች እና በአባል ሀገራት የሚመራ የኮፕ 32 ሂደትን ለመተግበር ያላትን ቁርጠኝነትም በድጋሚ አረጋግጠዋል። ሚኒስትሩ አክለውም በይዘትና ድርድር፣ በሎጂስቲክስና ኦፕሬሽን፣ በአጋርነት እንዲሁም ሚዲያና ኮሙኒኬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች በዝግጅት ረገድ የተመዘገቡት ተጨባጭ እድገቶችን አሳይተዋል።
ብክለትን በመከላከል ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣይ ትውልድ ለማውረስ የጋራ ጥረት ያስፈልጋል
Jul 15, 2026 239
ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ):-የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣይ ትውልድ ለማውረስ የጋራ ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባ የኢፌዴሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 3ኛው ዙር "የጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" የአካባቢን ብክለት መከላከል ክልላዊ የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በዲላ ከተማ ተካሂዷል።   ንቅናቄው ለቀጣይ ሦስት ወራት የሚተገበር ሲሆን የፕላስቲክና የድምፅ ብክለትን መከላከል እና የጎጂ ኬሚካል አጠቃቀምን መቀነስን ዓላማ ያደረገ ነው ተብሏል። የኢፌዴሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፍሬነሽ መኩሪያ በወቅቱ እንዳሉት የአካባቢ ብክለት በዜጎች የእለት ተዕለት ኑሮ ላይ ጫና እያሳደረ ነው። በተለይ የፕላስቲክና የድምፅ ብክለት እንዲሁም ጎጂ የኬሚካል ቆሻሻ ተጽኖው ከፍተኛ መሆኑን አንስተው፣ የጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ ንቅናቄ የህብረተሰቡ ግንዛቤን በማሳደግ ችግሩን እያቀለለ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ የከተማና የገጠር የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትና የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የአካባቢ ብክለትን ከመከላከል ባለፈ ጽዱ ኢትዮጵያን ለመገንባት እያስቻሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ንቅናቄው ለቀጣይ ሦስት ወራት የሚተገበር ሲሆን የህብረተሰቡን ተሳትፎ ማጠናከር እንዲሁም ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም ሀብት መፍጠርን ጨምሮ ተግባራዊ የመፍትሔ እርምጃዎች ይወሰዳሉ ብለዋል። በዚህም የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ጽዱ ኢትዮጵያ ለቀጣይ ትውልድ ለማውረስ የጋራ ጥረትን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ገልጸዋል። ለቀጣይ ትውልድ ንጹህ እና ጤነኛ አካባቢን ለመፍጠር የጋራ ጥረትን ማስቀጠል እንደሚገባ ያነሱት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቴ ግጄ ናቸው።   በክልሉ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ዘላቂ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አንስተው ንቅናቄው የዚሁ አካል ነው ብለዋል። ህብረተሰቡ ቆሻሻና ብክለትን በመጸየፍ ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ ለማውረስ የሚደረገውን ጥረት እንዲያግዝም ጥሪ አቅርበዋል። በንቅናቄ መድረኩ ላይ የዘርፉ አመራሮች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ተማሪዎች እና ባለድርሻዎች ተገኝተዋል።    
በዞኑ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የሚሸፍኑ ችግኞት ይተከላሉ
Jul 15, 2026 309
ደሴ ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በሰሜን ወሎ ዞን በክረምቱ በሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የሚሸፍኑ ችግኞች እንደሚተከሉ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የሰሜን ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተገኝ አባተ ለኢዜአ እንደገለጹት፣የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዞኑ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል።   መርሃ ግብሩ የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ ፣ የአፈር ለምነት እንዲመለስ ፣በለሙ ተፋሰሶች ለወጣቱ የሥራ እድል እንዲፈጠር እና ምርታማነት እንዲያድግ ማድረጉን ነው የገለጹት። በዘንድሮው ክረምትም ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ 169 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል። ከሚተከሉት ችግኝ ውስጥ ሁለት ነጥብ ሶስት ሚሊዮን የሚሆነው የፍራፍሬ መሆኑን ጠቁመው ይህም የአርሶ አደሩንና የወጣቱን ዘላቂ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። ለዚህም የጉድጓድ ቁፋሮና ሌሎች ተያያዥ የቅደመ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ ለተከላ ዝግጁ የማድረግ ስራ መሰራቱን አስረድተዋል።   የሚተከለውን ችግኝ ከግጦሽና ከሰው ንክኪ በመጠበቅ የጽድቀት ምጣኔው ለማሳደግም ህብረተሰቡ የድርሻውን እንዲወጣ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ህብረተሰቡም ባለፉት ዓመታት ካለማቸው ተፋሰሶች እያገኘ ያለውን ጥቅም ለማስፋትም በያዝነው ክረምት በችግኝ ተከላው በንቃት ለመሳተፍ እንደተነሳሳም ተናግረዋል። በዞኑ ራያ ቆቦ ወረዳ 08 የአራዱም ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ሰይድ ይመር፤ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞችን በማፍላት በማሳቸው ላይ ተክለው ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። ዘንድሮም ከአንድ ሺህ በላይ የማንጎ፣ አቮካዶና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞችን ማዘጋጀታቸውን ጠቁመው ከተከላ የሚተርፈውን ሽጠው ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። በሰሜን ወሎ ዞን ባለፈው ክረምት ከተተከለው ችግኝ ውስጥ 78 በመቶ መጽደቁን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 19727
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 12808
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 11603
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 11498
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ ማኛ ወርቅ፤ ከተንጣለለው የጎጃም ማሳ ወደ ዓለም ገበያ
Jul 14, 2026 754
በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞኑ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የጤፍ ምርት ከሚገኝባቸው አካባቢዎች መካከል ይጠቀሳል። ለዚህ ስኬት የተፈጥሮ ጸጋው ብቻ ሳይሆን የአርሶ አደሮች ትብብር፣ ዘመናዊ የእርሻ አሰራርና የገበያ ትስስር መጠናከር ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። የተንጣለለው የምስራቅ ጎጃም ማሳ በጤፍ ተሸፍኖ ማየት ስሜትን ይገዛል። በማሳው መካከል ደግሞ አርሶ አደሮች በጋራ እየሰሩ መመልከት ከትውልድ ትውልድ የተላለፈ የመረዳዳትና ለሺህ ዘመናት ለዘለቀ አስተራረስ አብነት ነው። የጎጃም ጤፍ በጥራቱ ቢታወቅም፣ ምርቱን በተሻለ ዋጋ ለመሸጥ የሚያስችል የገበያ ትስስር ውስን ነበር። አርሶ አደሩ በብዙ ድካም ያመረተውን ምርት ለደላሎች በዝቅተኛ ዋጋ ለመሸጥ ይገደዳል። በምርቱ ላይ የሚፈጠረው እሴትም እምብዛም ነው።   ዛሬ ግን ያ ታሪክ እየተለወጠ ይመስላል። በደብረ ማርቆስ ከተማ የተቋቋመውና የማኛ ጤፍ ዱቄትን ወደ ዓለም ገበያ መላክ የጀመረው ፋብሪካ የአርሶ አደሩን ምርት በቀጥታ በመቀበል ወደ እሴት የሚቀይር ድልድይ ሆኗል። ከእርሻ ወደ ፋብሪካ፣ ከፋብሪካ ወደ ውጭ ገበያ የሚዘልቀው ይህ የእሴት ሰንሰለት የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማሳደግ አዲስ የለውጥ ምዕራፍን ከፍቷል። የማኛ ጤፍ ዱቄት ማምረቻ ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ ሰማኸኝ ጌታቸው እንደሚገልጹት፣ ፋብሪካው በቀን በአማካይ ከ600 እስከ 800 ኩንታል ጤፍ የሚፈጭ ሲሆን፥ ሥራ በጀመረባቸው ጥቂት ወራት ውስጥ 600 ቶን እሴት የተጨመረበት ጤፍ ለውጭ ገበያ አቅርቧል። በዚህም አንድ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለሀገር አስገኝቷል። ይህ አሃዝ የጤፍ ምርት በፋብሪካ እሴት ሲጨምር የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ ጥቅም በግልጽ ያሳያል ብለዋል። ከዚህ በላይ ደግሞ ፋብሪካው ለ70 የሚጠጉ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩ የግብርና ልማት ከኢንዱስትሪ ጋር ሲሰናሰል የሚፈጠረውን ተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያመለክታል። ይህ ማለት አንድ የጤፍ ሰብል ከማሳ እስከ ውጭ ገበያ ድረስ በሚያደርገው ጉዞ በርካታ የሥራ ዕድሎችን፣ የገቢ ምንጮችንና የኢኮኖሚ እሴቶችን ይፈጥራል ማለት ነው። በምስራቅ ጎጃም ዞን ትርፍ አምራች ከሆኑ አካባቢዎች መካከል በደጀን ወረዳ የሚገኙ አርሶ አደሮችም ይህንን ለውጥ በቀጥታ እየተጠቀሙበት ነው። በክላስተር ማረስ የምርት ጥራትን በማሻሻል ጉልህ ጠቀሜታ ያስገኛል። ኢዜአ ከዚህ ቀደም በወረዳው በኩታ ገጠም የጤፍ ምርት ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን በጎበኘበት ወቅት የተመለከተው እውነትም ይህንኑ ነው። ፋብሪካው ደግሞ ከተጠቃሚነት ላይ ተደማሪ ጠቀሜታ የሚያገኙበትን ዕድል ፈጥሯል።   በደጀን ወረዳ በክላስተር ተደራጅተው ጤፍን በስፋትና በጥራት ከሚያመርቱ አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር መኩሪያው ታደለ አንዱ ሲሆኑ፤ የኩታ ገጠም እርሻ የጉልበት ወጪን በመቀነስ የምርት ጥራትና ብዛትን በማሳደግ ከፍተኛ ውጤት እንደሚያስገኝ ይገልፃሉ። በክላስተር ማምረት በአንድ ጊዜ መዝራት፣ መከታተልና መሰብሰብ በመቻሉ የምርት ብክነትን መቀነስ እንደተቻለም ሌላው አርሶ አደር ሸጋው ከፍያለው ያብራራሉ።   እንደ እርሳቸው ገለጻም፤ አርሶ አደሮች በአንድነት መስራታቸው የግብርና ሥራዎችን በወቅቱ ለማከናወን አስችሏል። ይህም በምርታማነት ላይ ቀጥተኛ አወንታዊ ተፅዕኖን ፈጥሯል። በተመሳሳይ አቶ ውዱ ሞሱ እንደሚሉት፤ የአርሶ አደሮች መተባበር ከዘር እስከ ምርት አሰባሰብ ድረስ በሁሉም ሂደት ውጤታማ አድርጓቸዋል። ምርቱ ሲደርስም በደቦ በመሆን በአጭር ጊዜ በመሰብሰብ የጊዜና የጉልበት ብክነትን አስቀርቷል።   የአርሶ አደሩ ስኬትም በማሳ ብቻ የሚቆም አይደለም። ከምርቱ መገኛ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው ደብረ ማርቆስ ከተማ የተቋቋመው የማኛ ጤፍ ዱቄት ማምረቻ ፋብሪካ ሥራ መጀመሩ የደጀንና የአካባቢውን አርሶ አደሮች ከማሳ በቀጥታ ወደ ዓለም ገበያ የሚያገናኝ አዲስ የእሴት ሰንሰለት ፈጥሯል። ከዚህ ቀደም ጤፍ እንደ ጥሬ ምርት ብቻ ይሸጥ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ ግን በፋብሪካ ተበጥሮ፣ ተፈጭቶ፣ በዘመናዊ መልክ ታሽጎ እሴት ተጨምሮ ወደ ውጭ ገበያ እየተላከ ነው። የደብረ ማርቆስ ከተማም በዚህ ሂደት የኢንዱስትሪ ማዕከል እየሆነች ነው። በከተማዋ የሚገኙ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የአካባቢውን ጥሬ እቃ በመጠቀም እሴት የሚጨምሩ በመሆናቸው ግብርናን ከኢንዱስትሪ ጋር የሚያስተሳስሩ የልማት ሞዴሎች እየሆኑ መጥተዋል። ይህም ለጎጃም ብቻ ሳይሆን ለመላው ኢትዮጵያ የግብርና ሽግግር አቅጣጫን የሚያሳይ ጠቃሚ ልምድ ነው። የኢትዮጵያ ጤፍ በባህላችን ያለውን ክብር ተጠብቆ በዓለም ገበያም ተፈላጊነቱን እያሳደገ ነው። ይህን ዕድል በተሻለ መንገድ ለመጠቀም የምርት ጥራትን ማሻሻል፣ የማቀነባበር አቅምን ማስፋት፣ የአርሶ አደሩን የገበያ ትስስር ማጠናከርና ተመሳሳይ የእሴት ጭማሪ ኢንዱስትሪዎችን በሌሎች አምራች አካባቢዎች ማስፋፋት ቀጣዩ የልማት ምዕራፍ ይሆናል። ከጎጃም የተንጣለለ የእርሻ ማሳ የሚነሳው የጤፍ እህል ዛሬ በፋብሪካ እሴት ተጨምሮ ወደ ዓለም ገበያ እየተጓዘ ነው፤ ይህም የኢትዮጵያ ግብርና ከባህላዊ አመራረት ወደ እሴት ጭማሪ ኢኮኖሚ እየተሸጋገረ መሆኑን የሚያሳይ ተጨባጭ ውጤት ሆኗል።   የደብረ ማርቆስ ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ተመስገን ተድላ፣ ከተማዋ ለኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ተመራጭ እየሆነች የመጣችው በቂ ጥሬ ዕቃ፣ የሰው ኃይል፣ የተሻለ የመጓጓዣ አገልግሎትና የሰላም ሁኔታ በመኖሩ መሆኑን ያብራራሉ። በተለይም የጎጃም አካባቢ የግብርና ሃብት ለእሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎች ጠንካራ መሠረት እየፈጠረ መሆኑን ይጠቅሳሉ። በለውጡ ዓመታት 253 የአምራች ኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ መግባታቸውና አብዛኞቹ ወደ ምርት መሸጋገራቸው የአካባቢው ኢኮኖሚ እያደገ መምጣቱን ያሳያል። ከእነዚህ መካከል የጤፍ ማቀነባበሪያ ፋብሪካው የጎጃም ማኛ ወርቅ የሆነውን የጤፍ ምርት እሴት ጨምሮ ወደ ዓለም ገበያ በማቅረብ ለአርሶ አደሩ፣ ለከተማዋና ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ተጨባጭ ጥቅም የሚያስገኝበትን አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል ይላሉ። በዚህ መልኩ በምስራቅ ጎጃም ዞን ያለውን ሰፊ የጤፍ ምርት በደብረ ማርቆሱ ፋብሪካ እሴት ተጨምሮ ወደ አውሮፓና አሜሪካ ገበያ መድረሱ የኢትዮጵያ ግብርና ከጥሬ ምርት ሽያጭ ወደ እሴት ጭማሪ፣ ከአካባቢ ገበያ ወደ ዓለም ገበያ እየተሸጋገረ መሆኑን በግልጽ ያሳያል። ይህም ጤፍ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የሚያጠናክር ስትራቴጂያዊ ሀብት መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን አብራርተዋል።  
ለብሩህ ነገዋ በአዲስ ምዕራፍ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ
Jul 14, 2026 497
ለብሩህ ነገዋ በአዲስ ምዕራፍ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ በሙሴ መለሰ ረጅም ታሪክ፣ቱባ ባህልና ሕብረ-ብሔራዊነት መለያዋ የሆኑት ኢትዮጵያ፣ የነገ ተስፋዋን አስተማማኝ ለማድረግ አዲስ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል ይበልጥ ብሩህ ለማድረግ ሀገራዊ ምክክር ቁልፍና ታሪካዊ ሚና ይጫወታል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በመላ ሀገሪቱ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ አጀንዳዎችን የመሰብሰብ ስራ ያጠናቀቀ ሲሆን ነገ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በይፋ ይጀመራል። ኮሚሽኑ በመላ ሀገሪቱ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡትን ሀሳቦችን በማደራጀት ለዋናው ሀገራዊ ምክክር የሚቀርቡ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን በይፋ ለይቷል። እነዚህም የሀገር ግንባታ ታሪካዊ ሂደቶች፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች የአዲስ አበባ እና የድሬደዋ ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር፣ እንዲሁም የሰላም ግንባታ ናቸው። ስምንቱን መሠረታዊ አጀንዳዎች መነሻ በማድረግ የሚደረገው ውይይት፣ የፖለቲካ መረጋጋትን ከመፍጠር ባለፈ ለአስተማማኝ የኢኮኖሚ እድገትና ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። ምክክሩ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ያለው ፋይዳ እጅግ የጎላ ነው።ባለፉት የታሪክ ሂደቶች የተፈጠሩ ቅሬታዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በሰላማዊ ውይይት በመፍታት፣እርስ በርስ ለመደማመጥ እና ታሪካዊ ቁስሎችን በይቅርታ ለመፈወስ የሚያስችል ዋነኛ መንገድ ነው። ከጠመንጃና ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሀሳብ የበላይነት የሚነግስበትን፣አለመግባባቶችና ልዩነቶች በሰላማዊ ውይይትና በንግግር የሚፈቱበትን ባህል ያሰፍናል።ይህም ልዩነቶችን በመቀበል በአንድነትና በጋራ መኖር የሚያስችሉ የጋራ እሴቶችና ሀገራዊ መግባባቶች ለማጠናከር ይረዳል። ከዚህም ባለፈ፣ምክክሩ ለተቋማዊ እድገትና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዋነኛ ምሰሶ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ መልካም አጋጣሚን ይፈጥራል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ የሚጀመረውን ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አስመልክቶ ዛሬ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ምክክሩ ፍቱን የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን፣ የእኛን እና የመጪውን ትውልድ እጣ ፈንታና የወደፊት ተስፋ ሙሉ በሙሉ የሚወስን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ጭምር ነው ሲሉ ገልጸውታል። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፣ዛሬ ሀገራችን የምትሻው ጠመንጃ ያነገቡ ሳይሆን በሀሳብ ብስለት፣ በእውነት፣ በዕውቀትና በጽናት ታጥቀው የተሰናዱ የሰላም ታጋዮችን ነው ያሉ ሲሆን እኛ ዛሬም እንደ ትናንቱ በታላቅ የድል ዋዜማ ላይ እንገኛለን፤ ምክንያቱም የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ ማሸነፍ አይቀሬ ነው ብለዋል። ይህንን በጎ ዕድል ለመጠቀምም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንነትና በኃላፊነት ስሜት በመሳተፍ ለሀገር ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ሀገራዊ ምክክር የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል በራስ አቅምና ጥበብ ለመወሰን የሚያስችል ትልቅ እድል ነው።የኢትዮጵያ መጻኢ ተስፋና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ጋር የተሳሰረ ነው። ባለፉት የታሪክ ሂደቶች ውስጥ የተፈጠሩ ቅሬታዎችን በንግግር መፍታት፣ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሃሳብ የበላይነት የሚነግስበትን ምቹ መደላድል ይፈጥራል። ዛሬ በምክክሩ ጠረጴዛ ዙሪያ የሚታየው የመነጋገር እና የመደማመጥ ባህል እንዲሁም ችግሮችን በውይይት ብቻ የመፍታት አማራጭ የተሻለች ኢትዮጵያን እውን የሚያደርግ ታሪካዊ መሰረት ይጥላል።
የሌማት ትሩፋት ሀገራዊ ስኬት- ከአመጋገብ ለውጥ እስከ ገቢ ምንጭ
Jul 13, 2026 708
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፦ለብዙ ኢትዮጵያውያን ወተት፣ እንቁላል፣ ማርና ሥጋ በምግብ ገበታ የማይገኙ፣ ለረጅም ዓመታት የቅንጦት ያህል የሚታዩና በቂ ምርት ባለመኖሩም በገበያ ላይ በስፋት የማይገኙ ነበሩ። ይህንን እውነታ ለመቀየርና የዜጎችን የሥርዓተ ምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመረው የሌማት ትሩፋት ሀገራዊ መርሃ ግብር ዛሬ ላይ ትልቅ ተስፋና ተጨባጭ ውጤት እያሳየ ይገኛል። ቀደም ሲል ትኩረት አጥቶ የነበረውን የእንስሳት ተዋጽኦ ልማት በቅንጅትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ ረገድ በአካባቢው ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል። በግብርና ሚኒስቴር መረጃ መሠረት መርሃ ግብሩ ከመጀመሩ በፊት የነበረው 7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ሊትር የወተት ምርት ዘንድሮ 15 ነጥብ 7 ቢሊዮን ሊትር መድረሱ፣ በዓመት የሚሰራጨው የዶሮ ጫጩት ከ26 ሚሊዮን ወደ 184 ሚሊዮን ማደጉ እንዲሁም የእንቁላል ምርት ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ወደ 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን ከፍ ማለቱ የዚሁ ሀገራዊ ስኬት ማሳያዎች ናቸው። ይህ የተጀመረው አበረታች ሂደት እንደ ወተት፣ ማር፣ ሥጋ፣ አሳ እና እንቁላል ያሉ ምርቶች የቅንጦት ሳይሆኑ የዜጎች የዕለት ተዕለት የሥርዓተ ምግብ አካል እንዲሆኑ በማስቻል ረገድም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። መርሐግብሩ በቢሾፍቱ ከተማና አካባቢዋ ለሚኖሩ በርካታ ዜጎችም የአመጋገብ ሥርዓትን ከመቀየር ባለፈ፣ የኢኮኖሚ አቅማቸውን የለወጠ የሕይወት ጉዞን ፈጥሮላቸዋል። አቶ ከፈለኝ ጫላ ቀደም ሲል በመንግሥት ሥራ በደመወዝ ነበር የሚተዳደሩት። የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ላይ ዜጎች እንዲሳተፉ ጥሪ ሲቀርብ ግን የቀደማቸው አልነበረም።   ገንዘብ በብድር በማመቻቸት በአንድ የወተት ላም ሥራቸውን ጀመሩ። በአሁኑ ወቅት የወተት ላሞቻቸውን ቁጥር 15 ማድረስ ችለዋል። የአካባቢው አስተዳደርና ባለሙያዎች ያደረጉላቸው ተከታታይ ድጋፍና ክትትል አሁን ለደረሱበት ውጤት እንዲበቁ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳበረከተላቸው ያነሳሉ አቶ ከፈለኝ። የራሳቸውን ኑሮ ከመቀየር ባለፈ፣ የሚያመርቱትን ወተት ለአካባቢው ማኅበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን በማረጋጋት ረገድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። የተመጣጠነ አመጋገብን እንድንከተል የሌማት ትሩፋት ትልቅ ለውጥ አምጥቷል የሚሉት አቶ ከፈለኝ፥ በተጨማሪም በመስኩ ለሌሎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል። ሌላኛው በዚሁ መርሃ ግብር ሕይወታቸው የተቀየረው ሥራ ፈጣሪ አቶ ጌቱ ብሩ ናቸው። እሳቸው ደግሞ በተቀናጀ የዶሮና የዓሣ ልማት ዘርፍ ላይ ነው የተሰማሩት።   የሌማት ትሩፋት ያመጣላቸው በረከት ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከመጥቀም አልፎ የንግድ አድማሳቸውን አስፍቶላቸዋል። ከልማቱ በሚያገኙት የምርት ውጤት የራሳቸውን ሆቴል መክፈት የቻሉ ሲሆን፣ ለበርካታ ዜጎችም የሥራ ዕድል ፈጥረዋል። "ለሆቴላችን የምግብ ግብዓት የሚሆነውን ምርት የምናቀርበው ከራሳችን የዶሮና የዓሣ እርባታ ማዕከል ነው" የሚሉት አቶ ጌቱ፣ ዘርፉ ሰፊና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት የሚቻልበት መሆኑን ይመሰክራሉ። አቶ ጌቱ እቅዳቸው እዚህ ላይ ብቻ አያበቃም፤ በቀጣይ የሌማት ትሩፋት ምርቶችን እሴት ጨምረው ለከተሞች ከማቅረብ ባለፈ ወደ ውጭ ሀገር ለመላክና ለሀገር የውጭ ምንዛሬ የማስገኘት ውጥን አላቸው። ሌሎችም በዚህ ሥራ ላይ ቢሰማሩ ከራሳቸው አልፈው ሀገርንና ወገንን መለወጥ እንደሚችሉም ነው የጠቆሙት። በተመሳሳይ በዶሮ እርባታ ሥራ ላይ የተሰማሩት አቶ ደረጄ አበበ መርሃ ግብሩ ከፍተኛ ገቢ እንዲያገኙ እንዳስቻላቸው ይናገራሉ።   የዶሮ እንቁላል በተመጣጣኝ ዋጋ ለአካባቢው ማኅበረሰብ በስፋት በማቅረብ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ጠቅሰዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር)፥ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡበትና የዜጎችን የምግብና ሥርዓተ ምግብ አቅም እያሳደገ የሚገኝ ኢኒሼቲቭ ነው ብለዋል።   ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ሀገራዊ ጥረት ለማሳካት የእንስሳት ሀብት ልማት ዘርፍ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ጠቅሰዋል። አክለውም፤ ኢኒሼቲቩ በቤተሰብ ደረጃ የዶሮ እርባታ ባህል እንዲሆን በማድረግ፣ በተለይም ሕፃናትና እናቶች የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ በማስቻል ረገድ መሠረታዊ ለውጥ እያመጣ መሆኑንና ምርቶች በስፋት ለገበያ እንዲቀርቡ በማስቻል ረገድ ትርጉም ያለው ውጤት ማምጣቱን ገልጸዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Jul 12, 2026 825
አዲስ አበባ፤ ሀምሌ 5/2018 (ኢዜአ) ፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የኢትዮጵያ እመርታ በምሁራን እይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግብርና፣ ቱሪዝም፣ በመሠረተ-ልማትና በማህበራዊ ዘርፎች በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ እመርታ እየመጣ መሆኑን ገልጸዋል። የእርሳቸውን ማብራሪያ ተከትሎ ኢዜአ ያነጋገራቸው በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲንና የአግሪካልቸራል ኢኮኖሚክስ ባለሙያ ከዲር ጀማል (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት አቅጣጫን በመከተል አቅምን አካብቶ በተደመረ አቅም በማልማት ባለፉት አምስት አመታት የተመዘገበው ስኬት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።   በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት ሙሐመድ ኢብራሂም በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በብዝሃ ዘርፍ ላይ ያተኮረ መሆኑ በሁሉም ዘርፎች ተመጣጣኝ የሆነ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብ አግዟል ብለዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊና ስነሰብ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር)፤ መንግስት ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማስመዝገብ የነደፋቸው ፖሊሲዎች ሀገር ያላትን ጸጋዎች አልምቶ ለመጠቀም ወሳኝ ናቸው ብለዋል። የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማስፋፋትና ለማዘመን ከተያዙ ቁልፍ ዘርፎች መካከል የኢንዱስትሪው ክፍለ-ኢኮኖሚ ዋነኛውና የትኩረት ማዕከል መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ መጥቀሳቸውም ይታወሳል። ከለውጡ በፊት በሀገሪቱ የነበሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ከ47 በመቶ በታች እንደነበር ጠቅሰው፤ ለዚህም እንደ ፋይናንስ፣ መሬትና የኃይል አቅርቦት ችግሮች በምክንያትነት ይጠቀሱ እንደነበር ገልጸዋል። ይህንን ችግር ለመቅረፍ መንግሥት ልዩ ኮሚቴ በማቋቋም እያንዳንዱን ኢንዱስትሪ በመጎብኘትና ችግሮቻቸውን በየደረጃው ለመፍታት ባደረገው የተቀናጀ ጥረት፣ ቀድሞ የነበሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅማቸው ዛሬ ላይ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል፡፡ በድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር መስፍን መኮንን (ዶ/ር)፤ ባለፉት ዓመታት የውጭ ምንዛሬ እጥረት በትልቅ ተግዳሮትነት የቆየ ቢሆንም አሁን ላይ ግን ችግሩ በፍጥነት እየተቀረፈ ይገኛል ብለዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የግብርናና ምጣኔ ባለሙያ እና ተመራማሪ አደባ ገመቹ (ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ እንደ ስንዴ እና ሩዝ ያሉ ሰብሎችን በስፋት በማምረት ከውጭ የሚገባውን ምርት ለመቀነስና ለማስቀረት ስኬታማ ስራዎችን ማከናወኗን ገልጸዋል። የወላይታ ሶዶ እና የወሎ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን በበኩላቸው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የተከማቹ ችግሮችን ለመፍታት ያለውን ዕድል መጠቀም እንደሚገባ የገለጹትን ሃሳብ በመጋራት፤ ለኢዜአ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ምሁራኑ በኮሚሽኑ የተለዩት የምክክር አጀንዳዎች ሁሉንም አካታች አድርገው የተመረጡና ለቆዩ ሀገራዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት እንደሚያስችሉ ተናግረዋል። በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ትምህርት መምህርና ተመራማሪ ተሻለ ተገኔ (ዶ/ር) እንዳሉት በኮሚሽኑ የተለዩ ስምንት የምክክር አጀንዳዎች ለቅራኔ ምንጭ የሆኑ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ የዜጎችን አንድነት በማጠናከር ለሀገራቸው በጋራ እንዲቆሙ በማድረግ በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ አለው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የስነ ዜጋና ስነ ምግባር ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ጣሰው ታደሰ ናቸው። በወሎ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ተባባሪ ፕሮፌሰር ቴዎድሮስ ካሴ በበኩላቸው፤ የምክክር ኮሚሽኑ የለያቸው የመወያያ አጀንዳዎች ስር የሰደዱ ችግሮችን በመለየት መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። ለሰላም ለተዘረጉ እጆች ምላሽ የሰጡ ወጣቶች ስኬት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ከጥፋታችን ተምረን ለልማትና ለሰላም ግንባታ አርአያ በመሆን እየሰራን ነው ሲሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች የገለጹት በዚህ ሳምንት ነው። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የተሃዲሶ ስልጠና ወስደው ህብረተሰቡን ተቀላቅለው በልማት ስራ ላይ የተሰማሩ የቀድሞ ታጣቂዎችን የኢዜአ ሪፖርተር አነጋግሯቸዋል። የቀድሞ ታጣቂዎቹ፤ በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት ማህበረሰባቸውንም ይሁን ቤተሰባቸውን የጎዱበት አጋጣሚ ሲያስታውሱ ከፍተኛ ጸጸት የሚሰማቸው መሆኑን ገልጸዋል። በጫካ እንዲሰባሰቡ ያደረጓቸው አካላት ለዘረፋና ሃብት ማካበት እንጂ ለአላማ የተሰለፉ እንዳልሆኑ በመረዳታቸውም የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው የተሃዲሶ ስልጠና ወስደው ማህበረሰቡን መቀላቀላቸውን ተናግረዋል። ለሰላም ለተዘረጉ እጆች ምላሽ የሰጡት ወጣቶቹ የልማት አርበኛ እና የሰላም አምባሳደር ሆነው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እየመከረች ነው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን "ሀገራዊ የምክክር ጉባኤውን" ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ማካሄድ ይጀምራል። በምክክር ኮሚሽኑ በተለዩት ስምንት አንኳር አጀንዳዎች ላይ የኢትዮጵያ ህዝቦች በተወካዮቻቸው አማካኝነት ተመካክረው የሚያቀርቧቸው ምክረ ሀሳቦች በተግባር ተተርጉመው ዘላቂ መፍትሄ ይገኝባቸዋል ተብሎም ታስቧል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአማራ ክልል ሴቶች ማህበራት ፌዴሬሽን ለምክክሩ የተለዩ አጀንዳዎች የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በመፍታት በአሰባሳቢ ትርክት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት የሚያስችሉ ነጥቦች መሆናቸውን ገልጿል።   የፌዴሬሽኑ ዳይሬክተር ወይዘሮ እንየ ገነቱ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ ታሪካዊ እድል መሆኑን አንስተዋል። የአማራ ክልል ሴቶች ማህበራት ፌዴሬሽን በምክክር ሂደቱ እስካሁንም በንቃት መሳተፉን አውስተው በቀጣይም ለምክክር ጉባኤው መሳካት የበኩሉን ድርሻ ይወጣል ብለዋል። የዲጅታል አገልገሎት ለዘመናዊ የንግድ ስርአት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ''የተደራጀ የዲጂታል አገልግሎት ለዘመናዊ የንግድ አገልግሎት'' በሚል መርህ የሴክተር ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ አካሄዷል።   በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፤ በበጀት ዓመቱ የንግድ ዘርፉን ከማዘመን በተጨማሪ ዲጂታል አገልግሎቱን በማጠናከር ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል። በተለይም የተገልጋዩን ጊዜና ጉልበት ለሚቆጥቡ አገልግሎቶች ተደራሽነት የተደረጉ ጥረቶች ስኬታማ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ የንግድ ፈቃድና መሠል አገልግሎቶችን በኦን ላይን በመፈጸም የንግዱን ማህበረሰብ የአገልግሎት እርካታ 96 በመቶ ማድረስ ተችሏል ብለዋል። በበጀት ዓመቱ 805 ተጨማሪ የቅዳሜ እና ዕሁድ ገበያዎች መከፈታቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ በዚህም በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን ለማህበረሰቡ በቀጥታ ማቅረብ በመቻሉ ገበያው እየተረጋጋ መምጣቱን አንስተዋል። በበጀት ዓመቱ ወደ ውጭ ከተላኩ የተለያዩ ምርቶች ከ11 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ ማንሳታቸው ይታወሳል። ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሳምንቱ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በስፋት የተተገበረበትም ነው። የዘንድሮው ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሃሳብ በሀዋሳ ከተማ የተካሄደው በዚህ ሳምንት ነው።   የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት እንደገለጹት ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የመደጋገፍና የመረዳዳት እሴቶችን በማጎልበት ማህበራዊ ሃላፊነት በጋራ መወጣት የሚያስችል ነው። በመርሃ ግብሩ ወጣቶች የሚያከናውኗቸው የልማት ተግባራት ህዝቡን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።   በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ በበኩላቸው በጎነትና አብሮነት የማህበረሰቡ መልካም እሴት በመሆኑ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት በወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ወጣቶች እርስ በርስ ግንኙነታቸውን በማጠናከር ባከናወኗቸው ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎች ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው።   በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት 25 ሚሊዮን ወጣቶች በተለያዩ ዘርፎች በመሳተፍ ከ53 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ተግባራትን እንደሚያከናውኑም ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሰት ወረዳ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትም የክልሉ እና የዞኑ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል። በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ እንደገለፁት፤ የህዝቡን የነበረውን የቆየውን የመረዳዳት እሴትና ባህል ወደነበረበት ለመመለስ የክልሉ መንግስት እየሰራ ይገኛል።   ባለፉት የለውጥ ዓመታት በበጎ ፍቃድ አገለግሎት በቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶቾ፣ የአረጋውያን እንክብካቤን ጨምሮ በአቅመ ደካማ ቤት እድሳትና ግንባታ፣ በደም ልገሳ፣ በፅዳት፣ በውበትና በአረንጓዴ አሻራ ህዝቡ የነበረው ተሳትፎ ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን አመላክተዋል። ተስፋን እንትከል ሳምንቱ የክረምቱ ዝናብ ያየለበትና የእርሻውና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላው መርሃግብር በስፋት የተካሄደበት ሆኖ አልፏል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ጎን ለጎን ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ጋር በፓርላማ ጊቢ ከተከሉት ችግኝ ጀምሮ በመላ ሀገሪቷ በስፋት የተተከለበት ሳምንት ነው። በሳምንቱ የክልል አመራሮች፣ የተቋማት ተወካዮች፣ የከተማ አስተዳደሮች፣ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና የመንግስት ሰራተኞች እንዲሁም ነዋሪዎች ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች በስፋት ተክለዋል። 8 ቢሊዮን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች የሚተከሉበት የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቢሾፍቱ ሆረ አርሰዴ ሀይቅ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሐሳብ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ቦሎቄን በኩታ ገጠም በኦሮሚያ ክልል የአርሶ አደሮችን ገቢ ለማሳደግ የሚረዱ እና ለወጪ ንግድ የሚውሉ ምርቶችን በስፋት የማምረት ስራ ትኩረት ማግኘቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ገለጹ። በክልሉ ምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሰት ወረዳ ቦሎቄን በኩታ ገጠም የመዝራት ሥራ የክልሉ፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች በተገኙበት ተጀምሯል። በዚሁ ወቅት የቢሮ ኃላፊው አቶ ኃይሉ አዱኛ በክልሉ የግብርና ምርታማነትን በእጥፍ ከመጨመር ጎን ለጎን፣ የአርሶ አደሮችን ገቢ ለማሳደግ በወጪ ንግድ ምርቶች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ብለዋል። በዞኑ ቦሰት ወረዳ የዶንጎሬ ጪዮስ ቀበሌ የተጀመረው ቦሎቄን በኩታ ገጠም የመዝራት ሥራ ለዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው መሰል መልካም ተሞክሮዎች እንዲሰፉ ይደረጋል ነው ያሉት። በደቡብ ወሎ ዞኑ 15 የእርሻ ትራክተሮች ለአርሶ አደሩ የተከፋፈሉትም በዚሁ ሳምንት ነው።   የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮነን በርክክቡ ወቅት እንደገለጹት፤ በዞኑ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ግብርናውን በማዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ የተደረገው ጥረት አበረታች ውጤት ተመዘግቦበታል። ዞኑ በሜካናይዜሽን ለሚካሄድ የሰብል ልማት ምቹ መሆኑን ጠቁመው፣ በዚህም በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ ጥራትና ብዛት ያለው ምርት በማምረት ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የማዳበሪያ ስርጭት በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ አቶ ደረጀ ማንደፍሮ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ለዘንድሮው የመኸር ሰብል ልማት 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።   እስካሁን ባለው ሒደትም ከ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ወደ አካባቢው የገባ ሲሆን ከዚህ ውስጥም 4 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል የሚሆነውን ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል። የማዳበሪያ ስርጭቱ ቀድመው ለሚዘሩ አካባቢዎችንና በክረምት ለተሽከርካሪ አስቸጋሪ ለሆኑ አካባቢዎች ቅድሚያ በመስጠት የተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን በጎንደር ከተማ ገጠር ቀበሌዎች የተጀመረው ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር ግንባታ በአዲሱ በጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የከተማው አስተዳደር አስታወቀ፡፡ ከተማ አስተዳደሩ በ2019 በጀት ዓመት አሻጋሪ የእድገትና የዘላቂ የልማት እቅድ ዙሪያ ከአጋር አካላት ጋር የትውውቅ መድረክ አካሂዷል፡፡   በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ፕላንና ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ፋሲል አብዩ እንደተናገሩት የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ ሁለንተናዊ አገልግሎትን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት መሰረተ ልማትን በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ እና የግብርናውን ኢኮኖሚ ለማዘመንም ፋይዳው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል። በቅርቡ በጎንደር ከተማ በሳይ እና በሳቢያ የገጠር ቀበሌዎች በገጠር ኮሪደር የተገነባውን ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር በአዲሱ በጀት ዓመትም በሌሎች ቀበሌዎች ለማስፋት የቅድመ ዝግጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። በአስተዳደሩ ስር በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች 20 ሞዴል የገጠር መንድሮችን ለመገንባት ዝግጅት መጀመሩንም አቶ ፋሲል ጠቅስዋል። የማዕድን ሀብት ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፥ ሀገሪቱ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከወርቅ ማዕድን ዘርፍ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ታሪካዊ ገቢ ማስመዝገቧን ይፋ አድርገዋል። በማዕድን ዘርፍ የተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ እና ድጋፍ ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ማስቻሉንም አስታውሰዋል። የማዕድን ሀብት ክምችት ከሚገኝባቸው አካባቢዎች አንዱ የሆነው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም ከለውጡ ወዲህ ለዘርፉ በተሰጠው ትኩረት የማዕድን ምርት ዕድገት በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል።   የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ናስር ሙሐመድ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በክልሉ ወርቅን ጨምሮ በርካታ ማዕድናትን በማልማት የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ከመቻሉ በላይ ክልሉ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢም በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መምጣቱን አስታውቀዋል። ለአብነትም በ2018 በጀት ዓመት 8 ሺሕ 961 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መግባቱን ገልጸዋል። ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልልም በበጀት ዓመቱ 348 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መቅረቡን የክልሉ ማዕድን እና ኢነርጂ ኤጀንሲ አስታውቋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ወልያብ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 350 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ለማቅረብ ታቅዶ 348 ኪሎ ግራም ምርት ቀርቧል። በጥራትና በፍጥነት የፕሮጀክቶች ግንባታ በሶማሌ ክልል የተጠናቀቀውን የ2018 በጀት ዓመት የሴክተር ቢሮዎች የአፈጻጸም ግምገማ መድረክ በጅግጅጋ ከተማ ተካሂዷል።   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው ጊዜ በጥራት ተጠናቀው ለአገልገሎት እንዲበቁ ተገቢ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል። የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የክልሉ እና የሀገሪቱን ልማት ማፋጠን የሚችል ብቁ የሰው ሀይል እንዲያፈሩ የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎችም ይጠናከራሉ ሲሉ ተናግረዋል። መሰረተ ልማት ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ 40 ሺህ አዳዲስ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ይህን የተናገሩት የሞጆ-አዳማ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት በጀመረበት ወቅት ነው።   ፕሮጀክቱ ለ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ህዝብ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን አዳማ የንግድ፣ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማዕከል እንደመሆኗ፣ ፕሮጀክቱ ለሚቀጥሉት አስር ዓመታት የተሟላ አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ 40 ሺህ አዳዲስ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ከ25 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በአሁኑ ወቅትም ከእነዚሁ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ የጎዴና ቢቸና ከተሞች የውሃ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን አንስተዋል። ማጠቃለያ ሳምንቱ በሁሉም ክልሎቻችን መደበኛ የልማት፣ የማህብራዊ እና የሰላም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው የቀጠሉበትም ነበር። በሁሉም ክልሎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተሳካ ሁኔታ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በተመሳሳይ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኝ ተከላና የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በሁሉም ክልሎች እየተከናወነ ይገኛል።    
ትንታኔዎች
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 3954
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!  
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 3163
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ትላንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሳሰር - የመደመር መንግስት እይታ በቱሪዝም
Jul 1, 2026 3164
በዮሐንስ ደርበው ቱሪዝም ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመላው ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ በአህጉራችን አፍሪካም ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙበት ሃገራት እንዳሉ ይታወቃል። ቱሪዝም ከገቢነት ከኢኮኖሚያዊ እቅምነት ባለፈ ትውልድን ያስተሳስራል ብሄራዊ ትርክትን ለመገንባትም ያግዛል ። ትላንትን ከዛሬ ዛሬንም ከነገ ጋር የሚያስተሳስር ነው። “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግስት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ በማድረግም ይጠበቅባቸዋል።
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 6921
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው  
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 10109
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 20502
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 13544
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 19296
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 101176
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 76444
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 55740
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 53287
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 38442
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 38025
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 37511
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 36492
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 101176
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 76444
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 55740
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 53287
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 6397
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 4422
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም