ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር የክላስተር የፍራፍሬ ልማት ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተከናወነ
Apr 17, 2026 25
ደዋጨፋ፤ሚያዝያ 9/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደና በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የሚመራ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ በክላስተር የሚካሄድ የፍራፍሬ ልማት ችግኝ ተከላ አስጀምሯል። ከርዕሳነ መስተዳድሮቹ በተጨማሪ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ፣እንዲሁም በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር)ና ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ተገኝተዋል።   በተጨማሪም ሌሎች የክልል፣የዞን አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመርሃ ግብሩ ታድመዋል። በክልሉ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፣የዞኑ ስነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ለፍራፍሬ ልማት ምቹ ነው። ዞኑ በገፅና በከርሰ ምድር ውሃ የታደለ በመሆኑ ያለውን ጸጋ በመጠቀም የኩታ-ገጠም የፍራፍሬ ልማት ስራን በዛሬው እለት በይፋ መጀመሩን ገልጸዋል።   ይህም እስካሁን በተበጣጠሰ መልኩ ሲካሔድ የነበረውን የፍራፍሬ ልማት ወደ ኩታ ገጠም በማስፋት ለአገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ታልሞ እየተሰራ መሆኑን ያመላክታል ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም የአካባቢው አርሶ አደሮችን በማደራጀትና ግንዛቤ በመፍጠር የፍራፍሬ ልማት ስራ አዋጭ መሆኑን ከግንዛቤ አስገብተው ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
የሉሲ ሙዚየም ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በቅንጅት ይሰራል      
Apr 17, 2026 37
ሰመራ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ የሉሲ ሙዚየም ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በቅንጅት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ህይወት ሐይሉ ገለጹ። በአፋር ክልል የሚገነባው የሉሲ ሙዚየም ለአርኪኦሎጂስቶችና የታሪክ ተመራማሪዎች የዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የምርምር ማዕከል በመሆን ከማገልገሉ ባለፈ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ቱሪስቶችን በመሳብ የሀገሪቱን ገጽታ ለመገንባት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ቅርሰ ባለ ስልጣንና የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ በትናንትናው ዕለት የሉሲ ሙዚየም ግንባታ ፕሮጀክት የውል ስምምነት ማድረጋቸው ይታወሳል።   የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ህይወት ሐይሉ ለኢዜአ እነደገለጹት የሉሲ ሙዚየም ግንባታን በተያዘለት ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት በቅንጅት ይሰራል። ባለስልጣኑ ለፕሮጀክቱ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን የገለጹት ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ፣ በቀጣይነት ትላልቅ የምርምር ስራዎች የሚከናወኑበት ማዕከል እንደሚሆንም አስረድተዋል። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከዚህ ቀደም የሱልጣን ዓሊሚራህ ሐንፈሬ ቤተ-መንግስት ዕድሳትን ጨምሮ የተለያዩ የምርምር ስራዎችን ማከናወኑን ጠቅሰው፣ አሁንም ከሙዚየሙ ግንባታ ጋር ተያይዞ ተጓዳኝ ስራዎችን ለማከናወን ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።   በባለሰልጣኑ የቅርስ አስተዳደር መሪ ስራ አሰፈፃሚ ፀሃይ እሼቴ እንዳሉት፤ የሙዚየሙ መገንባት ለሃገርም ሆነ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የጎላ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ሙዝየሙ ቅርሶችና ሌሎች መረጃዎች በተገቢው ጥንቃቄ እንዲቀመጡና እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ የክልሉን ቅርሶች ለማደራጅት እንደሚያስችልም ጠቁመዋል። የሙዚየሙ ስራ መጀመር የሰው ዘር አመጣጥና የአፋርን ባህል ለማጥናት ለሚፈልጉ አካላት የመረጃ ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኀላፊ አቶ ኢብራሂም ሁመድ ናቸው።   የሙዚየሙ መገንባት የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ በማሳደግ የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንደሚያሳድገው አስረድተዋል።
በቡና ክላስተር የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ሊጠናከሩ ይገባል
Apr 17, 2026 47
አረካ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቡናን በክላስተር በማልማት የአርሶ አደሮችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመረው ተግባር መጠናከር እንዳለበት የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ ገብረመስቀል ጫላ ተናገሩ። ቡናን በክላስተር ማልማት ላይ ያተኮረ ክልላዊ የቡና ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዛሬ በወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ አቹራ ቀበሌ ተካሂዷል።   "የቡና ምርት ዕድገት ለኢኮኖሚያችን" በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደ የችግኝ ተከላ መርሀግብር ላይ ‎የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንደገለጹት፤ በመንግስት ትኩረት ከተሰጣቸው ብዝሃ የኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል ግብርና አንዱ ነው። ከግብርና ምርቶች መካከል ቡና የአንበሳውን ድርሻ እንደሚይዝ ጠቅሰው፣ ቡናን በክላስተር ለማልማት የተጀመረው ሥራ ልማቱን ከማዘመን ባለፈ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በእጥፍ ስለሚያሳድገው መጠናከር አለበት ብለዋል። ‎የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በማስፋፋትና የግብርና ስራውን በማዘመን ለምርታማነት መጨመር ሁሉም በተለይ የዘርፉ አመራር መረባረብ አለበት ሲሉም አስገንዝበዋል።   ህብረተሰቡ ውሃ ገብ ከሆኑ አካባቢዎች ባህር ዛፍና ያረጁ ቡናዎችን በመንቀልና በመጎንደል የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ እንዲሆን የባለሙያዎች ድጋፍ መጠናከር እንዳለበትም አሳስበዋል። ‎በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ ‎የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቡና ላይ መስራት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚኖረው አስተዋጽኦ የጎላ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል።   ለዚህም ‎ዘንድሮ በክልል አቀፍ ደረጃ ከ40 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኞች እንደሚተከሉ ጠቅሰው፣ በቡና ከሚለማው መሬትም 5 ሺህ ሄክታሩ በኩታ ገጠም እንደሚለማ አመልክተዋል። በክልሉ በባህር ዛፍ የተሸፈኑ ማሳዎችን በተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች የመቀየር ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ያሉት ኃላፊው ዘንድሮ ከሚተከሉ የቡና ችግኞች መካከል 34 ሚሊዮን የሚሆነው በተያዘው ሚያዚያ ወር የሚተከል ነው ብለዋል። ‎‎የቡና ልማቱ የአርሶ አደሩን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለብዙዎች የሥራ ዕድል እየፈጠረ ነው ያሉት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሠማ (ረ/ፕሮፌሰር) ናቸው። ‎ይህንን ለማጠናከር ለዘንድሮ የበልግ ወቅት ከ6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ዝግጅት፣ የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ፣ የኮምፖስት እና የጥላ ዛፎች ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።   ‎ከዚህ በተጨማሪ በዞኑ በልዩ ንቅናቄ 2ሺህ 253 ሄክታር የነባር ቡና ማሳ ዕድሳት ሥራ እና ከ2 ሺህ በላይ ሄክታር አዲስ የቡና ማሳ ዝግጅት ተከናውኗል ብለዋል። ‎‎በዞኑ በተለያዩ ክላስተሮች 1 ሺህ 207 ሄክታር ማሳ ላይ በኩታ ገጠም ቡና ተክሎ ለማልማት ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ ወደ ትግበራ መገባቱንም ጠቁመዋል። በዛሬው የተከላ መርሃ ግብር ከተሳተፉት ነዋሪዎች መካከል አቶ ዘለቀ ስኔቦ እና መጋቤ ተስፋዬ ሹኬ፤ ከዚህ ቀደም ቡናን በባህላዊ መንገድ ስለሚያመርቱ ከልማቱ ብዙም ተጠቃሚ እንዳልነበሩ አስታውሰዋል። ከዘርፉ ባለሙያዎች በተሰጣቸው ትምህርት መሰረት የባህር ዛፍ ቦታን በተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች በመተካታቸው የተሻለ ምርት ማግኘት መጀመራቸውን ተናግረዋል። በተለይ ቡናን በክላስተር ማልማት ድካምንና ያለአግባብ ይባክን የነበረን ጊዜ በመቀነስ ተጠቃሚነትን ስለሚያሳድግ አጠናክረው ለማስቀጠል መዘጋጀታቸውን ነው የገለጹት። በቡና ችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ ከክልል ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ሥራ ኃላፊዎችና የወረዳው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በክልሉ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዝግጅት ላይ ከሚገኙ ችግኞች መካከል 70 በመቶው የፍራፍሬ ችግኞች ናቸው 
Apr 17, 2026 51
በጋምቤላ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ልማት እየተዘጋጁ ከሚገኙት ችግኞች መካከል 70 ከመቶ የሚሆኑት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡ በክልሉ ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በ70 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ እንደሆነ ቢሮው ገልጿል። በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ ኬት ቾል ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚያግዙና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ላላቸው ችግኞች ትኩረት ተሰጥቷል።   በዚህም 70 በሚሆኑ የግልና የመንግስት የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች እየተዘጋጁ ከሚገኙት ችግኞች መካከል 70 ከመቶ የሚሆኑት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን ተናግረዋል። ከችግኞቹ መካከል ማንጎ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ ፣ ዘይቱናና ሎሚ ዋነኞቹ እንደሆኑም ገልጸዋል። ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ልማት እየተዘጋጁ ካሉት የፍራፍሬ ችግኞች ባለፈ ከአካባቢው የአየር ንብረት ጋር የሚጣጣሙ የደን ችግኞች እየተዘጋጁ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በበጋው ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የተከናወነባቸው ከዘጠኝ ሺህ ሄክታር በላይ የተራቆቱ አካባቢዎችን ስነ-ህይወት ለማልበስ የመረጣና የቦታ ልየታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።   በክልሉ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የተተከሉት የፍራፍሬና ሌሎች ችግኞች የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ከመቀየር ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ረገድ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙም ተናግረዋል። በቀጣይም በክረምቱ ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በሚያግዙ ችግኞች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
በጎንደር ከተማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 11 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ገብተዋል
Apr 17, 2026 61
ጎንደር ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በጎንደር ከተማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 11 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ። በከተማው በ400 ሚሊዮን ብር ወጪ በአንድ ባለሀብት የተገነባ የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ተመርቆ ስራ ጀምሯል። የመምሪያው ሃላፊ ግርማይ ልጃለም እንዳሉት፤ በዘንድሮው ዓመት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 20 መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ምርት ማምረት ለማሸጋገር እየተሰራ ነው። ባለፋት ዘጠኝ ወራት በተደረገ የተቀናጀ ጥረትም 10 መካከለኛና አንድ ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪ ወደ ማምረት እንዲገቡ መደረጉን ገልጸዋል። ወደ ምርት እንዲገቡ የተደረጉት ኢንዱስትሪዎችም በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ማምረት ላይ የተሰማሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የስራ ዕድል በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማሳደግ ያስቻሉ ሲሆን ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ እንደሆኑም ገልጸዋል።   አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ወደ ማምረት መሸጋገራቸውም ገበያን በማረጋጋት፣ ተኪ ምርቶችን በማምረትና የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንም አመልክተዋል። በከተማው የሰፈነው ሠላም አምራች ኢንዱስትሪዎቹ በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ እንዲገቡ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ያሉት ደግሞ የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው።   የከተማ አስተዳደሩ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የግንባታ መሬት ከማዘጋጀት ጀምሮ መሠረተ ልማቶችን በማሟላት ፈጥነው ወደ ስራ እንዲገቡ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል። የዘይት ፋብሪካው ባለቤት አቶ አደራጀው ገብረሚካኤል በበኩላቸው፤ ፋብሪካው በቀን 20 ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት የማምረት አቅም እንዳለው ተናግረዋል።   ፋብሪካው በቀን 400 ኩንታል አኩሪ አተር በጥሬ እቃነት የሚጠቀም ሲሆን ይህም በግብርና ስራ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች አስተማማኝ የገበያ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ለ30 ወገኖች የስራ እድል መፍጠሩን ጠቅሰው፤ 400 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ ከተማ አስተዳደሩ ባመቻቸው 7 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ መገንባቱንም ጠቁመዋል። በስነ ስርዓቱ ላይም የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የሚታይ
በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር የክላስተር የፍራፍሬ ልማት ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተከናወነ
Apr 17, 2026 25
ደዋጨፋ፤ሚያዝያ 9/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደና በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የሚመራ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ በክላስተር የሚካሄድ የፍራፍሬ ልማት ችግኝ ተከላ አስጀምሯል። ከርዕሳነ መስተዳድሮቹ በተጨማሪ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ፣እንዲሁም በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር)ና ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ተገኝተዋል።   በተጨማሪም ሌሎች የክልል፣የዞን አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመርሃ ግብሩ ታድመዋል። በክልሉ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፣የዞኑ ስነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ለፍራፍሬ ልማት ምቹ ነው። ዞኑ በገፅና በከርሰ ምድር ውሃ የታደለ በመሆኑ ያለውን ጸጋ በመጠቀም የኩታ-ገጠም የፍራፍሬ ልማት ስራን በዛሬው እለት በይፋ መጀመሩን ገልጸዋል።   ይህም እስካሁን በተበጣጠሰ መልኩ ሲካሔድ የነበረውን የፍራፍሬ ልማት ወደ ኩታ ገጠም በማስፋት ለአገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ታልሞ እየተሰራ መሆኑን ያመላክታል ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም የአካባቢው አርሶ አደሮችን በማደራጀትና ግንዛቤ በመፍጠር የፍራፍሬ ልማት ስራ አዋጭ መሆኑን ከግንዛቤ አስገብተው ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የማይበገር የምግብ ስርዓት እየገነባች ነው
Apr 17, 2026 78
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ያሏትን የተፈጥሮ ሀብቶች በሚገባ በማወቅና በማልማት ለዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የማይበገር የምግብ ስርዓት እየገነባች መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ። ላለፉት ጥቂት ዓመታት መንግሥት ተግባራዊ ባደረገው የባለብዙ ዘርፍ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠቱ፣ ዘርፉ አስደናቂ የምርት እድገትና መዋቅራዊ ሽግግር እያስመዘገበ ይገኛል። በተለይም በበጋ ስንዴ እና በመስኖ ልማት ረገድ በስፋት የተከናወኑት ተግባራት ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የስንዴ አምራች ሀገር እንድትሆን ያስቻሉ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ አፋጥኖታል። ይህ ስኬት ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የኢኮኖሚ ጥንካሬዋን እና የግብርና ምርታማነት አቅሟን በተግባር ያሳየ ሆኗል። የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት በተሟላ መልኩ ለማረጋገጥ የምርትና ምርታማነት እድገት መሰረታዊ ነው። ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ስንዴ ከውጭ ገዝታ ለማስገባት ታወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጪ ማስቀረት መቻሏን ገልጸዋል። መንግሥት የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመንና ምርትን ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት፣ በግዥ ከውጭ ይገባ የነበረውን ስንዴ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መተካት እንደተቻለ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። ይህ ታሪካዊ ስኬት የሀገሪቷን የውጭ ምንዛሬ ከመታደጉ ባለፈ ራስን በምግብ ለመቻል ለተያዘው ብሄራዊ ግብ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በምርምር፣ በግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና በተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም ረገድ ሰፊ ስራዎችን በማከናወን ላይ ትገኛለች ብለዋል። በተለይም የማዳበሪያ አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት የተጀመረው የፋብሪካ ግንባታ ተጠናቆ ወደ ስራ ሲገባ ከፍተኛ የኢኮኖሚ እና የምርታማነት ለውጥ እንደሚያመጣ ገልጸዋል። ምርታማነታቸው ከፍተኛ የሆነና በሽታን የመቋቋም አቅም ያላቸው ምርጥ ዘሮች በራስ የምርምር አቅም ማውጣት የሚያስችል የግብርና ምርምር ስርዓት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያላትን የመሬት፣የውሃ እና የሰው ሃይል አቅም በማቀናጀት ለግብርናው ዘርፍ የሚያስፈልጉ የሃይል እና የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ለማሟላት የምታደርገው ጥረት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ነው ያስገነዘቡት። አንድ ሀገር በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከሰቱ የጂኦፖለቲካ ለውጦች በነዳጅ አቅርቦትና በምግብ ሉዓላዊነት ላይ የሚያስከትሉትን ብርቱ ተጽዕኖ ለመቋቋም የሚያስችል ስራ በትኩረት መከናወን እንዳለበት አንስተዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋዎች በሚገባ ለይታ በማወቅና በማልማት፣ ማንኛውንም ወቅታዊ ዓለም አቀፍ ቀውስ መቋቋም የምትችል ጠንካራ ሀገር ለመገንባት በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ይህም ከውጭ የሚመጡ ተጽዕኖዎችን ተቋቁማ የምግብ ሉዓላዊነቷን በተገቢው መንገድ እንድታረጋግጥ የሚያስችላት መሆኑንም ገልጸዋል። የምግብ ሉዓላዊነቷን ያረጋገጠች ጠንካራ ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው ጥረት አርሶና አርብቶ አደሮች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉም ብለዋል።
ሪፎርሙ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ፈተናዎችን የመቋቋም አቅሙ እንዲጠናከር አድርጓል
Apr 17, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገር በቀል ሪፎርሙ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ፈተናዎችን የመቋቋም አቅሙን ማጠናከሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ (ዶ/ር) ገለጹ። የ2026 የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የፀደይ ወቅት ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ይገኛል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) አይኤምኤፍ “ከአዲሱ ዓለም አቀፍ ፋይናንስ ስነ-ምህዳር ጋር መጣጣም” በሚል ርዕስ ባዘጋጀው ከፍተኛ የፓናል ውይይት ላይ ተሳትፈዋል። በወቅቱም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አቅርቦት በተገደበበት በዚህ ወቅት፣ በሀገር በቀል የሪፎርም እርምጃዎች አማካኝነት ፈታኝ ሁኔታዎችን እንዴት እየተወጣች እንደምትገኝ አብራርተዋል። እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በንግግራቸው የኢትዮጵያን አጠቃላይ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርም ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል። ሪፎርሙ የምንዛሬ ተመን ማዕቀፍን ማጠናከር፣ የገንዘብ ፖሊሲን ማዘመን፣ የሀገር ውስጥ ሀብት አሰባሰብን ማሳደግ እና ኢኮኖሚው ይበልጥ በግል ዘርፍ የሚመራ እንዲሆን ለማድረግ የሚከናወኑ መዋቅራዊ ሪፎርሞችን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል።   የኢኮኖሚው የመቋቋም አቅም መጠናከር በወጪ ንግድ፣ በውጭ ምንዛሬ ክምችትና በገቢ አሰባሰብ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን የባንኩ ገዥ አመልክተዋል። ምንም እንኳን የኢትዮጵያ ሪፎርም በሀገር ውስጥ ባለቤትነት የሚመራ ቢሆንም፣ የልማት አጋሮች የሚያደርጉት የተቀናጀ ድጋፍ ለውጤታማነቱ አስፈላጊ መሆኑን ገዢው አስገንዝበዋል። በተለይም ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋት በግልጽ በሚታይበት በዚህ ወቅት፣ ሀገራዊ የልማት ጥረቶችን ለማሳካት የልማት አጋሮች የሚያደርጉት ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። ይህ የፓናል ውይይት ኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለመጠበቅ፣ ሪፎርሞችን ለማስቀጠል እና ተለዋዋጭ በሆኑ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች ውስጥ ይበልጥ ጠንካራና ሁሉን አቀፍ ኢኮኖሚ ለመገንባት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ያረጋገጠ ሆኗል። ገዢው በሀገር ደረጃ እያደገ የመጣውን የለውጥና የብልጽግና ፍላጎት በማንሳት፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተምሳሌት (Beacon) የመሆን ጉዞ ላይ እንደሆነች ገልጸዋል። በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አይበገሬነት አድናቆት እንዳገኘ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ
Apr 17, 2026 298
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራውና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፍተኛ አማካሪ አቶ ተክለወልድ አጥናፉንና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተው የኢትዮጵያ ልዑክ፣ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የፊስካል ጉዳዮች የስራ ዘርፍ ጋር የሥራ ውይይት አድርጓል። ውይይቱ በዋናነት ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለችውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ ግብር ለመደገፍ በሚሰጡ የቴክኒክ ድጋፎች ላይ ያተኮረ ነው። የመንግሥት የፋይናንስ አሠራርና የበጀት አጠቃቀም ግልጽነትን ማሻሻል እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥ ስጋቶችን ከሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕቅድና በጀት ጋር ማጣጣም በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም መክሯል። የታክስ ፖሊሲና አስተዳደርን በተመለከተ፣ የኢትዮጵያን የታክስ ሥርዓት ለማዘመን፣ የታክስ መሠረቱን ለማስፋት እንዲሁም በዲጂታላይዜሽንና በተቋማዊ አቅም ግንባታ አማካኝነት የታክስ ሕግ ተገዢነትን ለማሻሻል በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ሁለቱ ወገኖች ተወያይተዋል። የአይኤምኤፍ ቡድንም ኢትዮጵያ ፍትሃዊነትንና ቀልጣፋ የታክስ ሥርዓትን በማረጋገጥ ቀጣይነት ያለው የገቢ ዕድገት እንድታስመዘግብ የታለመ የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጧል።   የመንግሥት የልማት ድርጅቶች (SOE) ሪፎርምን በተመለከተ፣ ልዑኩ መንግሥት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን፣ የፋይናንስ ስርዓትን ለማጠናከር እንዲሁም የዋና ዋና የልማት ድርጅቶችን አፈጻጸምና ተጠያቂነት ለማሻሻል እያደረገ ያለውን ቀጣይነት ያለው ጥረት አስመልክቶ ገለጻ አድርጓል። አይኤምኤፍ በበኩሉ የተጀመሩ ጥረቶችን በማበረታታት፣ የፊስካል ስጋቶችን ለመቀነስ ጠንካራ የክትትል ማዕቀፎችና ግልጽ የሪፖርት አቀራረብ ሥርዓቶች ወሳኝ መሆናቸውን አጽንኦት ሰጥቷል። በፊስካል ግልጽነት ዙሪያ የተደረገው ውይይት የሕዝብ ፋይናንስ አስተዳደር ሥርዓቶችን ማጠናከር፣ የበጀት ተዓማኒነትን ማሻሻልና የፊስካል ሪፖርቶችን ከዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎች ጋር ማጣጣም በሚሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የኢትዮጵያ ልዑክም ግልጽነትና ተጠያቂነትን ማስፈን የሪፎርም አጀንዳ ዋና ምሰሶ መሆኑን በመግለጽ የመንግሥትን ቁርጠኝነት አረጋግጧል። ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ በሚሰጡ የቴክኒክ ድጋፎች ላይ፤ አይኤምኤፍ መንግሥት የአየር ንብረት ፖሊሲዎች ያሉበትን ደረጃ ለመገምገም የሚያደርገውን ጥረት እየደገፈ መሆኑ ተገልጿል። ሁለቱ ወገኖች የቴክኒክ ግንኙነቱን ለማሳደግና የኢትዮጵያ ሪፎርም ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለመደገፍ በቅርበት ለመሥራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። የኢትዮጵያ ልዑክ አይኤምኤፍ (IMF) ላሳየው ቀጣይነት ያለው አጋርነት፣ ለአቅም ግንባታና ለተቋማዊ ጥንካሬ ለሚያደርገው ድጋፍ ያለውን አድናቆት መግለጹን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ያላትን ልምድ ለአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አጋራች
Apr 16, 2026 927
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ ያካበተችውን ተጨባጭ ልምድ ለአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አባላት አጋርታለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የመሩትን የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት የሚኒስትሮች ስብሰባን አስመልክቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት የሊቀ መንበርነት ሚናዋን በብቃት እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል።   ዛሬ በበይነ-መረብ በተካሄደው በዚህ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ተሞክሮ ለማጋራት አመቺ ዕድል መፈጠሩን ቃል አቀባዩ አንስተዋል። ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለኢኮኖሚ፣ ለአስተዳደር እንዲሁም ለሰላምና ፀጥታ ሥራ ያለውን የጎላ ፋይዳ ለሚኒስትሮቹ አስገንዝበዋል ብለዋል። በተለይም ቴክኖሎጂው ግጭቶችን በመከላከል፣ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን በማስተላለፍ እና የሰላም ሂደቶችን በመደገፍ ረገድ ያለውን አበርክቶ አብራርተዋል። አምባሳደር ነብያት አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቅንጦት ሳይሆን ጠቃሚ የልማት መሣሪያ መሆኑን ኢትዮጵያ ተገንዝባለች ብለዋል። በዚህ ዘርፍም የተቀናጁ ተቋማትን በማቋቋም ህዝቡ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ቀልጣፋ ዲጂታል አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተሞክሮ እና በአቅም ግንባታ ረገድ እየተከናወነ ያለውን የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ በአብነት ለመድረኩ መቅረቡን ተናግረዋል። በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሻምፒዮን ሆነው መመረጣቸው፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ተሞክሮ ለሌሎች ሀገራት እንድታካፍል ትልቅ ዕድል መፍጠሩን አምባሳደሩ ገልጸዋል። አፍሪካ በቀደመው የኢንተርኔት ዘመን ዘግይታ መግባቷን ያስታወሱት ቃል አቀባዩ፤ አሁን ግን አህጉሪቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘመን ተገቢውን ቦታ በመያዝ የመሪነት ሚና እንዲኖራት ኢትዮጵያ ያላትን ጽኑ አቋም በመድረኩ ማንጸባረቋን ገልጸዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ለሀገርና ለሕዝብ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - አርሶ አደሮች 
Apr 17, 2026 156
ደሴ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ለሀገርና ለሕዝብ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በደቡብ ወሎ ዞን የተሁለደሬ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዘንድሮው ዓመት ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ በማውጣት የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ነው። ከዚህ ውስጥም የእጩዎች ምዝገባ የተጠናቀቀ ሲሆን የመራጭነት ምዝገባ ሂደት ደግሞ እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ/ም እንደሚካሔድም መገለጹ ይታወሳል፡፡ የወረዳው አርሶ አደሮች እንደሚሉት የምርጫ ካርድ በማውጣት በመጪው ምርጫ ላይ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት አድርገዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት ውስጥ አርሶ አደር ሰይድ ፈንታ፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ እና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል።   ይወክለኛል ያልኩትን ፓርቲ ወደ ስልጣን በማምጣት ሀገሪቷን እንዲመራ በካርዴ ለመወሰን እየተጠባበኩ እገኛለሁ ብለዋል። ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅም ከፀጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ነው የሚናገሩት። አርሶ አደር መሀመድ አደም በበኩላቸው፣ በምርጫው የሚጠበቀውን ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ነው የሚናገሩት።   በምርጫው ቀን ይጠቅመናል፣ ይበጀናል ለምንለው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠትና የዜግነት ግዴታችንን ለመወጣት እየተጠባበቅን እንገኛለን ሲሉም ተናግረዋል። ህገ-መንግስቱ ያጎናጸፈንን መብት ከመጠቀም ባለፈ ዴሞክራሲያዊ ልምምዱ በተሻለ መንገድ እንዲከወንና ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን የድርሻችንን እንወጣለን ነው ያሉት። የመራጭነት ካርድ መውሰድ ለምንፈልገው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠት ቁልፍ ተግባር ነው ያሉት ደግሞ አርሶ አደር ሉባባ መሀመድ ሲሆኑ ካርድ ያልወሰዱ ዜጎችም በቀሪ ጊዜያት ተመዝግበው ቢዘጋጁ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል።   በምርጫው ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
በዞኑ ለጠቅላላ ምርጫው የወጣቶችን ተሳትፎ ማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 
Apr 17, 2026 157
መቱ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የወጣቶችን ተሳትፎ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወኑ መሆናቸውን በኢሉአባቦር ዞን የሚገኙ የወጣት አደረጃጀቶች ገለጹ። የኢሉአባቦር ዞን ወጣቶች ፌዴሬሽን ሊቀመንበር አበበ ሆርዶፋ ለኢዜአ እንዳለው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የወጣቶች ተሳትፎ የጎላ ሚና አለው።   ለዚህም ለዞኑ ወጣቶች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድሕረ-ምርጫ ሂደቶች በንቃት እንዲሳተፉ የምርጫ ሥነ-ምግባር ትምህርቶች ላይ በማተኮር ግንዛቤ እንዲኖራቸው እየተደረገ ነው ብሏል። ምርጫ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ወጣቱ ለስኬታማነቱ የድርሻውን እንዲወጣ ለማድረግም ፌዴሬሽኑ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብሏል። የዞኑ ወጣቶች ማሕበር ሊቀመንበር ቢቂላ ኮይና በበኩሉ፤የዞኑ ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል። በተለይ የወጣቶችን አደረጃጀቶች በማጠናከር የመምረጥ፣ የመመረጥና የምርጫ ታዛቢነት መብታቸውንና የዜግነት ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ነው ያመለከተው። በዋናነትም ወጣቱ በምርጫው ሒደት በእውቀት ላይ የተመሠረተ ተሳትፎ እንዲኖረው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑን ተናግሯል። የወጣቱን ማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ነው የገለጸው።
ዜጎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በቀሪ ቀናት እንዲወስዱ የበኩላችንን ሚና እየተወጣን ነው
Apr 17, 2026 167
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9 /2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በቀሪ ቀናት በመውሰድ በምርጫው ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆኑን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ሲያካሂድ ቆይቷል። በተጨማሪም ቦርዱ የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሟል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥበት ዕለት ነው፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስቻላቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አህመድ ሁሴን ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ምርጫ ዜጎች ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን የሚያረጋግጡበት ሒደት ነው።   ይህም የዲሞክራሲ ባህልን በማዳበር ህዝብ የስልጣን ባለቤትነት መሆኑን በተግባር የሚረጋገጥበት እንደሆነ ተናግረዋል። ዜጎች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ አስቻይ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል። ምክር ቤቱም ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በምርጫው ዙሪያ ተከታታይ ውይይቶችን በማድረግ ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል። ለአብነትም በምርጫው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ያላቸውን የታዛቢነት ሚና እንዲወጡ በማድረግ ነጻ፣ተአማኒና ስኬታማ ምርጫ ለማከናወን የጋራ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችም በጠቅላላ ምርጫው ሒደት የዜጎች ተሳትፎ የተረጋገጠበት እንዲሆን ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል ብለዋል። እሸት ሀገር በቀል የህጻናትና ወጣቶች ልማት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ታረቀኝ እንደገለጹት፥ ምርጫ ዜጎች በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ የሚያጎለብቱበት ዕድል ነው።   በዚህም ድርጅቱ ዜጎች በቀሪ ቀናት የመራጭነት ካርድ በመውሰድ በምርጫው ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ፈጠራ እና መሰል ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል። በተለይም የምርጫ ካርድ መውሰድ መብት መሆኑን ማስገንዘብና በምርጫው ቀን ወጥተው እንዲመርጡ የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶች እየተሰጡ መሆኑን አብራርተዋል።   ሴቭ ዩር ሆሊ ላንድ የተሰኘ ሀገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ዳይሬክተር የማነህ ጉሽ በበኩላቸው፤ ዜጎች የመራጭነት ካርድን በመውሰድ በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ምርጫው ዲሞክራሲያዊና ሰላማዊ እንዲሆን ወጣቶች ያላቸውን የማይተካ ሚና እንዲወጡ በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ ስምምነቶች መደረጋቸውን ገልጸዋል። በቀሪ ቀናትም ዜጎች ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ካርድ እንዲወሰዱ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መምረጥ ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ ቀድመን አውጥተናል - አርሶ አደሮች
Apr 17, 2026 133
ደብረ ብርሃን ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ መምረጥ ህገ መንግስታዊ መብትና የዜግነት ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ ቀድመን አውጥተናል ሲሉ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የሚገኙ አርሶ አደሮች ገለጹ። አርሶ አደሮቹ ለኢዜአ እንዳሉት፤ መምረጥ ህገ መንግስታዊ መብትና የዜግነት ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ ቀድመው አውጥተዋል። አርሶ አደር ግዛው መኩሪያ በምርጫ መሳተፍ በህገ መንግስቱ የተሰጠንን ዴሞክራሲያዊ መብት የመጠቀም ዕድል ማግኘት ማለት ነው ብለዋል።   በዚህም ሰላምና ልማትን ያረጋግጣል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ቀድመው መውሰዳቸውን ገልጸዋል። እስካሁን የመራጭነት ካርድ ያልወሰዱ የአካባቢው ነዋሪዎች ከምርጫ ቦርድ የተሰጠውን ተጨማሪ ቀን በመጠቀም ካርዱን እንዲያወስዱም መክረዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አርሶ አደር ተፈሪ ጌታቸው በበኩላቸው መምረጥ ህገ መንግስታዊ መብትና የዜግነት ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ ቀድመን አውጥተናል ብለዋል።   በካርዳቸው ለሀገር ልማት ሰላምና እድገት ይጠቅማል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ እለቱን እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ገልጸዋል። አቶ አርጋው ዘለቀ በበኩላቸው ምርጫ የህዝብ የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጫና የስልጣኔ መገለጫ መሆኑን በመገንዘብ ካርድ ማውጣታቸውን ገልጸዋል።   ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻችንን እንወጣለን ያሉት ደግሞ አርሶ አደር ደረጀ መሰለ ናቸው።   በምርጫው በቀጣይ አምስት ዓመት ያስተዳድረኛል፤ ይበጀኛል ብለው ያመኑትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችል የመራጭነት ካርድ አውጥተው እለቱን እየተጠባበቁ መሆኑም ገልጸዋል።
በኦሮሚያ ክልል አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ ነው 
Apr 17, 2026 198
ቢሾፍቱ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወሉ አብዲ ገለጹ። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ አጠቃላይ የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በበርካታ ዘርፎች ውጤታማ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። በተለይም በክልሉ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቀነስ ተጨባጭ ውጤት እየተገኘበት ነው ብለዋል። የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትም በ5 ከተሞች በሙከራ ደረጃ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ በመሆኑ፣ ተሞክሮውን የማስፋት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በሁለተኛው ምዕራፍ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱን ወደ 26 ከተሞች ማስፋት ተችሎ አንዳንዶቹ አገልግሎት መጀመራቸውን ገልጸው፤ በሦስተኛው ምዕራፍ ደግሞ በ60 ከተሞች ለማስጀመር እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቁመዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያገኙ ዜጎች ከ97 በመቶ በላይ እርካታ እንዳላቸው የገለጹት አቶ አወሉ፤ ይህ አርአያነት ያለው ሥራ ተስፋፍቶ ሕዝቡ የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ በቁርጠኝነት እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል። ለሥራው ስኬታማነትም ቴክኖሎጂን፣ የሰው ኃይልን፣ የሥራ ቦታንና አሠራርን በማመቻቸት ረገድ ሰፊ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። አመራሩ ወደ ሕዝቡ ቀርቦ እንዲያገለግልም፣ የጉዳይ ፈጻሚ ቀናትን ከመለየት ባለፈ በወረዳዎችና በቀበሌዎች በተደረገው ሪፎርም ማኅበረሰቡ የሚፈልገውን አገልግሎት በቅርበት እንዲያገኝ መመቻቸቱን ጠቁመዋል። የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ እና ውጤታማ ማድረግ እንዲቻልም የመልካም አስተዳደር ችግር በሚፈጥሩ ሰራተኞች ላይ የተለያዩ የእርምት እርምጃዎች መወሰዳቸውን አንስተዋል። በሌላ በኩል በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ237 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸው፤ በቀጣይም የክልሉን ገቢ ለማሳደግ ለግብር ከፋዮች ግንዛቤ የመፍጠርና የገቢ ምንጮችን የመፈተሽ ስራ ይጠናከራል ብለዋል። በተመሳሳይ በክልሉ በበጀት ዓመቱ ከ28 ሺህ 800 በላይ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆኑን ተናግረው፤ ከእነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል 21 ሺህ የሚሆኑት በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት የሚሆኑ ናቸው ብለዋል።
በጠቅላላ ምርጫው ለሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚነት ለሚሰራ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል
Apr 16, 2026 1296
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ለሴቶችና ወጣቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የጋምቤላ ከተማ ወጣቶች ገለጹ። ወጣቶቹ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ለመራጭነት የሚያበቃቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱም ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ከሰጡ የጋምቤላ ከተማ ወጣቶች መካከል ቤዱና ኡከች፤ እየተቃረበ ባለው 7ኛ ዙር ጠቅላላ ምርጫ በተለይም ለሴቶችና ለወጣቶች ተጠቃሚነት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀቷን ተናግራለች።   ለዚህም ለመራጭነት የሚያበቃትን ካርድ መውሰዷንና ሌሎች እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆኑ ወጣቶችም ካርድ እንዲወስዱ እየቀሰቀሰች መሆኗን ጨምራ ገልፃለች። ለሴቶችና ወጣቶች መብትና ጥቅም የሚሰራ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቷን የተናገረችው ደግሞ ወጣት ኛጆክ ኮንግ ናት።   በምትኖርበት ቀበሌ ወጣቶችና ሴቶች የምርጫ ካርድ በመውሰድ ይጠቅመኛል የሚሉትን ፓርቲ እንዲመርጡ እየሰራች መሆኗንም ገልፃለች። ወጣት ካሰች ታፈሰ በበኩሏ፤ዴሞክራሲያዊ መብቷን ተጠቅማ ይበጀኛል የምትለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ቀደም ብላ ለመራጭነት የሚያበቃትን ካርድ ወስዳለች።   በምርጫውም ለሴቶችና ወጣቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይሰራል ለምትለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምጿን ለመስጠት መዘጋጀቷን ተናግራለች።
የሚበጀንን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ በመውሰድ ተዘጋጅተናል- ነዋሪዎች
Apr 16, 2026 775
ሰቆጣ ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ በመውሰድ ተዘጋጅተናል ሲሉ የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ነዋሪዎች ገለጹ። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ በመውሰድ ተዘጋጅተዋል። በብሔረሰብ አስተዳደሩ የሰቆጣ ወረዳ ባጊሚላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር አበራ ዘገዬ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን ካርድ ማውጣታቸውን ተናግረዋል።   ምርጫ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመንግስት ስልጣን የሚያዝበት በመሆኑ ይበጀናል ይጠቅመናል ያልነውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። ሁሉም መምረጥ የሚችል ዜጋ የመራጭነት ካርድ ሊያወጣ እንደሚገባ የመከሩት አርሶ አደር አበራ የሚበጃቸውን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫውን እለት በጉጉት እየጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል። በሰሃላ ወረዳ የ01 ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ጥሩወርቅ ሰርፀ በበኩላቸው፤ የመራጭነት ካርድ በማውጣት የዜግነት ሃላፊነታቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።   ካርዱን ለማውጣትም የአካባቢያቸውን ሴቶች በመቀስቀስና አብሮ በመሄድ በጋራ ማውጣታቸውን ጠቁመው በካርዳቸው የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል። የሚፈልጉትን የፖለቲካ ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ማውጣታቸውን የገለጹት ደግሞ የሰቆጣ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ካሳ አበባው ናቸው። ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ምርጫ ጠንካራና ሰላማዊ አገር ለመገንባት መሰረት በመሆኑ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ የዜግነት ግዴታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።   በቀሪ ቀናትም የምርጫ ካርድ ያላወጣው ነዋሪ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመሄድ ተመዝግቦ ካርዱን በእጁ መያዝ እንዳለበት አስተያየት ሰጪዎቹ አመልክተዋል። ግንቦት 24/2018 ዓ/ም ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ እየተካሄደ ያለው የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዚያ 14/2018 ዓ/ም መራዘሙ ይታወቃል።
የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋት ፓርቲዎች የፖለሲ አማራጫቸውን በነጻና በሰላማዊ መንገድ ለህዝቡ እንዲያስተዋውቁ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Apr 16, 2026 813
ወልቂጤ፤ ሚያዚያ 8/2018 (ኢዜአ):-የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋት የፖለሲ አማራጫቸውን በነጻና በሰላማዊ መንገድ ለህዝብ ለማስተዋወቅ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በጉራጌ ዞን የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ ሃላፊዎች ገለጹ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የጉራጌ ዞን አስተባባሪ አቶ ደምስ ገብሬ ለኢዜአ እንደገለጹት አሳታፊ ዴሞክራሲ ሥርዓት መገንባት ፍትሀዊ ምርጫን ለማድረግ ወሳኝ ነው። በጉራጌ ዞን የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር በመጠቀም ነፃና ሰላማዊ ምርጫ ለማከናወን የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በእስካሁኑ የምርጫ ሂደት የታዩ ጉድለቶችን ፓርቲዎች በውይይትና በመነጋገር እየፈቱ መሆናቸውን አብራርተዋል። የፖለቲካ መህዳሩ መስፋት ፓርታዎቹ ርዕዮተ ዓለማቸውን እና የተለያዩ ፕሮግራማቸውን ለህዝብ በነጻነት ለማስተዋወቅና ከደጋፊዎቻቸው ጋር ለመምከር ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል። በዞኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህጋዊ መንገድን ተከትለው በምርጫው አሸናፊ ለመሆን በነጻነት እየተፎካከሩ መሆናቸውን ያነሱት ደግሞ የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢና በብልፅግና ፓርቲ የዞኑ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አለማየሁ ገብረመስቀል ናቸው። ፓርቲያቸው በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊና አሳታፊ እንዲሆን የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እየተደረገ ነው ያሉት አቶ አለማየሁ፣ የተለያዩ መገናኛ ብዙሀንን በመጠቀም የፓርቲውን የፖሊሲ አማራጮች ለህዝብ ማስተዋወቃቸውን ገልጸዋል። ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትህ ፓርቲ የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አብዱልአዚዝ ሙሰማ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዘንድር ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋቱ ተናግረዋል። ይህም እንደፓርቲ ያላቸውን የፖሊሲ አማራጮች በተለያየ መንገድ ለህዝብ በነጻነት ለማቅረብ እንዳስቻለቸው ገልጸው፣ ፓርቲው የዘንድሮ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሀዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለአገር ይጠቅማል ያሉትን ሀሳብ በሰለጠነ መንገድ እያቀረቡ መሆናቸውን ነው የጠቆሙት። የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሕግን ባከበረ መንገድ ጠንካራ ተሳትፎ ማድረግ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጎለብት መሰረት መሆኑን ተረድተው በእዚሁ አግባብ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የምርጫ ክርክሩም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅምና የዜጎችን ክብር ባስጠበቀ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል።    
ፖለቲካ
ለሀገርና ለሕዝብ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - አርሶ አደሮች 
Apr 17, 2026 156
ደሴ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ለሀገርና ለሕዝብ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በደቡብ ወሎ ዞን የተሁለደሬ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዘንድሮው ዓመት ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ በማውጣት የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ነው። ከዚህ ውስጥም የእጩዎች ምዝገባ የተጠናቀቀ ሲሆን የመራጭነት ምዝገባ ሂደት ደግሞ እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ/ም እንደሚካሔድም መገለጹ ይታወሳል፡፡ የወረዳው አርሶ አደሮች እንደሚሉት የምርጫ ካርድ በማውጣት በመጪው ምርጫ ላይ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት አድርገዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት ውስጥ አርሶ አደር ሰይድ ፈንታ፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ እና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል።   ይወክለኛል ያልኩትን ፓርቲ ወደ ስልጣን በማምጣት ሀገሪቷን እንዲመራ በካርዴ ለመወሰን እየተጠባበኩ እገኛለሁ ብለዋል። ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅም ከፀጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ነው የሚናገሩት። አርሶ አደር መሀመድ አደም በበኩላቸው፣ በምርጫው የሚጠበቀውን ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ነው የሚናገሩት።   በምርጫው ቀን ይጠቅመናል፣ ይበጀናል ለምንለው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠትና የዜግነት ግዴታችንን ለመወጣት እየተጠባበቅን እንገኛለን ሲሉም ተናግረዋል። ህገ-መንግስቱ ያጎናጸፈንን መብት ከመጠቀም ባለፈ ዴሞክራሲያዊ ልምምዱ በተሻለ መንገድ እንዲከወንና ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን የድርሻችንን እንወጣለን ነው ያሉት። የመራጭነት ካርድ መውሰድ ለምንፈልገው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠት ቁልፍ ተግባር ነው ያሉት ደግሞ አርሶ አደር ሉባባ መሀመድ ሲሆኑ ካርድ ያልወሰዱ ዜጎችም በቀሪ ጊዜያት ተመዝግበው ቢዘጋጁ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል።   በምርጫው ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
በዞኑ ለጠቅላላ ምርጫው የወጣቶችን ተሳትፎ ማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 
Apr 17, 2026 157
መቱ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የወጣቶችን ተሳትፎ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወኑ መሆናቸውን በኢሉአባቦር ዞን የሚገኙ የወጣት አደረጃጀቶች ገለጹ። የኢሉአባቦር ዞን ወጣቶች ፌዴሬሽን ሊቀመንበር አበበ ሆርዶፋ ለኢዜአ እንዳለው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የወጣቶች ተሳትፎ የጎላ ሚና አለው።   ለዚህም ለዞኑ ወጣቶች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድሕረ-ምርጫ ሂደቶች በንቃት እንዲሳተፉ የምርጫ ሥነ-ምግባር ትምህርቶች ላይ በማተኮር ግንዛቤ እንዲኖራቸው እየተደረገ ነው ብሏል። ምርጫ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ወጣቱ ለስኬታማነቱ የድርሻውን እንዲወጣ ለማድረግም ፌዴሬሽኑ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብሏል። የዞኑ ወጣቶች ማሕበር ሊቀመንበር ቢቂላ ኮይና በበኩሉ፤የዞኑ ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል። በተለይ የወጣቶችን አደረጃጀቶች በማጠናከር የመምረጥ፣ የመመረጥና የምርጫ ታዛቢነት መብታቸውንና የዜግነት ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ነው ያመለከተው። በዋናነትም ወጣቱ በምርጫው ሒደት በእውቀት ላይ የተመሠረተ ተሳትፎ እንዲኖረው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑን ተናግሯል። የወጣቱን ማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ነው የገለጸው።
ዜጎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በቀሪ ቀናት እንዲወስዱ የበኩላችንን ሚና እየተወጣን ነው
Apr 17, 2026 167
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9 /2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በቀሪ ቀናት በመውሰድ በምርጫው ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆኑን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ሲያካሂድ ቆይቷል። በተጨማሪም ቦርዱ የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሟል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥበት ዕለት ነው፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስቻላቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አህመድ ሁሴን ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ምርጫ ዜጎች ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን የሚያረጋግጡበት ሒደት ነው።   ይህም የዲሞክራሲ ባህልን በማዳበር ህዝብ የስልጣን ባለቤትነት መሆኑን በተግባር የሚረጋገጥበት እንደሆነ ተናግረዋል። ዜጎች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ አስቻይ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል። ምክር ቤቱም ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በምርጫው ዙሪያ ተከታታይ ውይይቶችን በማድረግ ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል። ለአብነትም በምርጫው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ያላቸውን የታዛቢነት ሚና እንዲወጡ በማድረግ ነጻ፣ተአማኒና ስኬታማ ምርጫ ለማከናወን የጋራ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችም በጠቅላላ ምርጫው ሒደት የዜጎች ተሳትፎ የተረጋገጠበት እንዲሆን ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል ብለዋል። እሸት ሀገር በቀል የህጻናትና ወጣቶች ልማት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ታረቀኝ እንደገለጹት፥ ምርጫ ዜጎች በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ የሚያጎለብቱበት ዕድል ነው።   በዚህም ድርጅቱ ዜጎች በቀሪ ቀናት የመራጭነት ካርድ በመውሰድ በምርጫው ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ፈጠራ እና መሰል ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል። በተለይም የምርጫ ካርድ መውሰድ መብት መሆኑን ማስገንዘብና በምርጫው ቀን ወጥተው እንዲመርጡ የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶች እየተሰጡ መሆኑን አብራርተዋል።   ሴቭ ዩር ሆሊ ላንድ የተሰኘ ሀገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ዳይሬክተር የማነህ ጉሽ በበኩላቸው፤ ዜጎች የመራጭነት ካርድን በመውሰድ በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ምርጫው ዲሞክራሲያዊና ሰላማዊ እንዲሆን ወጣቶች ያላቸውን የማይተካ ሚና እንዲወጡ በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ ስምምነቶች መደረጋቸውን ገልጸዋል። በቀሪ ቀናትም ዜጎች ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ካርድ እንዲወሰዱ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መምረጥ ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ ቀድመን አውጥተናል - አርሶ አደሮች
Apr 17, 2026 133
ደብረ ብርሃን ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ መምረጥ ህገ መንግስታዊ መብትና የዜግነት ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ ቀድመን አውጥተናል ሲሉ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የሚገኙ አርሶ አደሮች ገለጹ። አርሶ አደሮቹ ለኢዜአ እንዳሉት፤ መምረጥ ህገ መንግስታዊ መብትና የዜግነት ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ ቀድመው አውጥተዋል። አርሶ አደር ግዛው መኩሪያ በምርጫ መሳተፍ በህገ መንግስቱ የተሰጠንን ዴሞክራሲያዊ መብት የመጠቀም ዕድል ማግኘት ማለት ነው ብለዋል።   በዚህም ሰላምና ልማትን ያረጋግጣል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ቀድመው መውሰዳቸውን ገልጸዋል። እስካሁን የመራጭነት ካርድ ያልወሰዱ የአካባቢው ነዋሪዎች ከምርጫ ቦርድ የተሰጠውን ተጨማሪ ቀን በመጠቀም ካርዱን እንዲያወስዱም መክረዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አርሶ አደር ተፈሪ ጌታቸው በበኩላቸው መምረጥ ህገ መንግስታዊ መብትና የዜግነት ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ ቀድመን አውጥተናል ብለዋል።   በካርዳቸው ለሀገር ልማት ሰላምና እድገት ይጠቅማል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ እለቱን እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ገልጸዋል። አቶ አርጋው ዘለቀ በበኩላቸው ምርጫ የህዝብ የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጫና የስልጣኔ መገለጫ መሆኑን በመገንዘብ ካርድ ማውጣታቸውን ገልጸዋል።   ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻችንን እንወጣለን ያሉት ደግሞ አርሶ አደር ደረጀ መሰለ ናቸው።   በምርጫው በቀጣይ አምስት ዓመት ያስተዳድረኛል፤ ይበጀኛል ብለው ያመኑትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችል የመራጭነት ካርድ አውጥተው እለቱን እየተጠባበቁ መሆኑም ገልጸዋል።
በኦሮሚያ ክልል አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ ነው 
Apr 17, 2026 198
ቢሾፍቱ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወሉ አብዲ ገለጹ። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ አጠቃላይ የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በበርካታ ዘርፎች ውጤታማ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። በተለይም በክልሉ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቀነስ ተጨባጭ ውጤት እየተገኘበት ነው ብለዋል። የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትም በ5 ከተሞች በሙከራ ደረጃ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ በመሆኑ፣ ተሞክሮውን የማስፋት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በሁለተኛው ምዕራፍ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱን ወደ 26 ከተሞች ማስፋት ተችሎ አንዳንዶቹ አገልግሎት መጀመራቸውን ገልጸው፤ በሦስተኛው ምዕራፍ ደግሞ በ60 ከተሞች ለማስጀመር እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቁመዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያገኙ ዜጎች ከ97 በመቶ በላይ እርካታ እንዳላቸው የገለጹት አቶ አወሉ፤ ይህ አርአያነት ያለው ሥራ ተስፋፍቶ ሕዝቡ የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ በቁርጠኝነት እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል። ለሥራው ስኬታማነትም ቴክኖሎጂን፣ የሰው ኃይልን፣ የሥራ ቦታንና አሠራርን በማመቻቸት ረገድ ሰፊ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። አመራሩ ወደ ሕዝቡ ቀርቦ እንዲያገለግልም፣ የጉዳይ ፈጻሚ ቀናትን ከመለየት ባለፈ በወረዳዎችና በቀበሌዎች በተደረገው ሪፎርም ማኅበረሰቡ የሚፈልገውን አገልግሎት በቅርበት እንዲያገኝ መመቻቸቱን ጠቁመዋል። የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ እና ውጤታማ ማድረግ እንዲቻልም የመልካም አስተዳደር ችግር በሚፈጥሩ ሰራተኞች ላይ የተለያዩ የእርምት እርምጃዎች መወሰዳቸውን አንስተዋል። በሌላ በኩል በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ237 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸው፤ በቀጣይም የክልሉን ገቢ ለማሳደግ ለግብር ከፋዮች ግንዛቤ የመፍጠርና የገቢ ምንጮችን የመፈተሽ ስራ ይጠናከራል ብለዋል። በተመሳሳይ በክልሉ በበጀት ዓመቱ ከ28 ሺህ 800 በላይ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆኑን ተናግረው፤ ከእነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል 21 ሺህ የሚሆኑት በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት የሚሆኑ ናቸው ብለዋል።
በጠቅላላ ምርጫው ለሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚነት ለሚሰራ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል
Apr 16, 2026 1296
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ለሴቶችና ወጣቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የጋምቤላ ከተማ ወጣቶች ገለጹ። ወጣቶቹ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ለመራጭነት የሚያበቃቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱም ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ከሰጡ የጋምቤላ ከተማ ወጣቶች መካከል ቤዱና ኡከች፤ እየተቃረበ ባለው 7ኛ ዙር ጠቅላላ ምርጫ በተለይም ለሴቶችና ለወጣቶች ተጠቃሚነት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀቷን ተናግራለች።   ለዚህም ለመራጭነት የሚያበቃትን ካርድ መውሰዷንና ሌሎች እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆኑ ወጣቶችም ካርድ እንዲወስዱ እየቀሰቀሰች መሆኗን ጨምራ ገልፃለች። ለሴቶችና ወጣቶች መብትና ጥቅም የሚሰራ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቷን የተናገረችው ደግሞ ወጣት ኛጆክ ኮንግ ናት።   በምትኖርበት ቀበሌ ወጣቶችና ሴቶች የምርጫ ካርድ በመውሰድ ይጠቅመኛል የሚሉትን ፓርቲ እንዲመርጡ እየሰራች መሆኗንም ገልፃለች። ወጣት ካሰች ታፈሰ በበኩሏ፤ዴሞክራሲያዊ መብቷን ተጠቅማ ይበጀኛል የምትለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ቀደም ብላ ለመራጭነት የሚያበቃትን ካርድ ወስዳለች።   በምርጫውም ለሴቶችና ወጣቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይሰራል ለምትለው የፖለቲካ ፓርቲ ድምጿን ለመስጠት መዘጋጀቷን ተናግራለች።
የሚበጀንን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ በመውሰድ ተዘጋጅተናል- ነዋሪዎች
Apr 16, 2026 775
ሰቆጣ ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ በመውሰድ ተዘጋጅተናል ሲሉ የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ነዋሪዎች ገለጹ። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ በመውሰድ ተዘጋጅተዋል። በብሔረሰብ አስተዳደሩ የሰቆጣ ወረዳ ባጊሚላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር አበራ ዘገዬ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን ካርድ ማውጣታቸውን ተናግረዋል።   ምርጫ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመንግስት ስልጣን የሚያዝበት በመሆኑ ይበጀናል ይጠቅመናል ያልነውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። ሁሉም መምረጥ የሚችል ዜጋ የመራጭነት ካርድ ሊያወጣ እንደሚገባ የመከሩት አርሶ አደር አበራ የሚበጃቸውን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫውን እለት በጉጉት እየጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል። በሰሃላ ወረዳ የ01 ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ጥሩወርቅ ሰርፀ በበኩላቸው፤ የመራጭነት ካርድ በማውጣት የዜግነት ሃላፊነታቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።   ካርዱን ለማውጣትም የአካባቢያቸውን ሴቶች በመቀስቀስና አብሮ በመሄድ በጋራ ማውጣታቸውን ጠቁመው በካርዳቸው የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል። የሚፈልጉትን የፖለቲካ ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ማውጣታቸውን የገለጹት ደግሞ የሰቆጣ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ካሳ አበባው ናቸው። ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ምርጫ ጠንካራና ሰላማዊ አገር ለመገንባት መሰረት በመሆኑ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ የዜግነት ግዴታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።   በቀሪ ቀናትም የምርጫ ካርድ ያላወጣው ነዋሪ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመሄድ ተመዝግቦ ካርዱን በእጁ መያዝ እንዳለበት አስተያየት ሰጪዎቹ አመልክተዋል። ግንቦት 24/2018 ዓ/ም ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ እየተካሄደ ያለው የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዚያ 14/2018 ዓ/ም መራዘሙ ይታወቃል።
የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋት ፓርቲዎች የፖለሲ አማራጫቸውን በነጻና በሰላማዊ መንገድ ለህዝቡ እንዲያስተዋውቁ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Apr 16, 2026 813
ወልቂጤ፤ ሚያዚያ 8/2018 (ኢዜአ):-የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋት የፖለሲ አማራጫቸውን በነጻና በሰላማዊ መንገድ ለህዝብ ለማስተዋወቅ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በጉራጌ ዞን የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ ሃላፊዎች ገለጹ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የጉራጌ ዞን አስተባባሪ አቶ ደምስ ገብሬ ለኢዜአ እንደገለጹት አሳታፊ ዴሞክራሲ ሥርዓት መገንባት ፍትሀዊ ምርጫን ለማድረግ ወሳኝ ነው። በጉራጌ ዞን የተፈጠረውን ምቹ የፖለቲካ ምህዳር በመጠቀም ነፃና ሰላማዊ ምርጫ ለማከናወን የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በእስካሁኑ የምርጫ ሂደት የታዩ ጉድለቶችን ፓርቲዎች በውይይትና በመነጋገር እየፈቱ መሆናቸውን አብራርተዋል። የፖለቲካ መህዳሩ መስፋት ፓርታዎቹ ርዕዮተ ዓለማቸውን እና የተለያዩ ፕሮግራማቸውን ለህዝብ በነጻነት ለማስተዋወቅና ከደጋፊዎቻቸው ጋር ለመምከር ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል። በዞኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህጋዊ መንገድን ተከትለው በምርጫው አሸናፊ ለመሆን በነጻነት እየተፎካከሩ መሆናቸውን ያነሱት ደግሞ የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢና በብልፅግና ፓርቲ የዞኑ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አለማየሁ ገብረመስቀል ናቸው። ፓርቲያቸው በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊና አሳታፊ እንዲሆን የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እየተደረገ ነው ያሉት አቶ አለማየሁ፣ የተለያዩ መገናኛ ብዙሀንን በመጠቀም የፓርቲውን የፖሊሲ አማራጮች ለህዝብ ማስተዋወቃቸውን ገልጸዋል። ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትህ ፓርቲ የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አብዱልአዚዝ ሙሰማ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዘንድር ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋቱ ተናግረዋል። ይህም እንደፓርቲ ያላቸውን የፖሊሲ አማራጮች በተለያየ መንገድ ለህዝብ በነጻነት ለማቅረብ እንዳስቻለቸው ገልጸው፣ ፓርቲው የዘንድሮ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሀዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለአገር ይጠቅማል ያሉትን ሀሳብ በሰለጠነ መንገድ እያቀረቡ መሆናቸውን ነው የጠቆሙት። የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሕግን ባከበረ መንገድ ጠንካራ ተሳትፎ ማድረግ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጎለብት መሰረት መሆኑን ተረድተው በእዚሁ አግባብ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የምርጫ ክርክሩም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅምና የዜጎችን ክብር ባስጠበቀ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል።    
ማህበራዊ
የሉሲ ሙዚየም ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በቅንጅት ይሰራል      
Apr 17, 2026 37
ሰመራ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ የሉሲ ሙዚየም ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በቅንጅት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ህይወት ሐይሉ ገለጹ። በአፋር ክልል የሚገነባው የሉሲ ሙዚየም ለአርኪኦሎጂስቶችና የታሪክ ተመራማሪዎች የዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የምርምር ማዕከል በመሆን ከማገልገሉ ባለፈ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ቱሪስቶችን በመሳብ የሀገሪቱን ገጽታ ለመገንባት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ቅርሰ ባለ ስልጣንና የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ በትናንትናው ዕለት የሉሲ ሙዚየም ግንባታ ፕሮጀክት የውል ስምምነት ማድረጋቸው ይታወሳል።   የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ህይወት ሐይሉ ለኢዜአ እነደገለጹት የሉሲ ሙዚየም ግንባታን በተያዘለት ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት በቅንጅት ይሰራል። ባለስልጣኑ ለፕሮጀክቱ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን የገለጹት ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ፣ በቀጣይነት ትላልቅ የምርምር ስራዎች የሚከናወኑበት ማዕከል እንደሚሆንም አስረድተዋል። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከዚህ ቀደም የሱልጣን ዓሊሚራህ ሐንፈሬ ቤተ-መንግስት ዕድሳትን ጨምሮ የተለያዩ የምርምር ስራዎችን ማከናወኑን ጠቅሰው፣ አሁንም ከሙዚየሙ ግንባታ ጋር ተያይዞ ተጓዳኝ ስራዎችን ለማከናወን ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።   በባለሰልጣኑ የቅርስ አስተዳደር መሪ ስራ አሰፈፃሚ ፀሃይ እሼቴ እንዳሉት፤ የሙዚየሙ መገንባት ለሃገርም ሆነ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የጎላ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ሙዝየሙ ቅርሶችና ሌሎች መረጃዎች በተገቢው ጥንቃቄ እንዲቀመጡና እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ የክልሉን ቅርሶች ለማደራጅት እንደሚያስችልም ጠቁመዋል። የሙዚየሙ ስራ መጀመር የሰው ዘር አመጣጥና የአፋርን ባህል ለማጥናት ለሚፈልጉ አካላት የመረጃ ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኀላፊ አቶ ኢብራሂም ሁመድ ናቸው።   የሙዚየሙ መገንባት የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ በማሳደግ የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንደሚያሳድገው አስረድተዋል።
በክልሉ በአካልና በአዕምሮ ብቁ የሆነ ትውልድ ለማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Apr 17, 2026 122
ሐረር፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በአካልና በአዕምሮ ብቁ የሆነ ትውልድ ለማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ተናገሩ። "በአካል የበቃ በአዕምሮ የነቃ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና" በሚል መሪ ሐሳብ የሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ 2ኛው ክልል አቀፍ የትምህርት ቤቶች ሊግና የመምህራን ስፖርት ውድድር ተጀመረ።   በውድድሩ መክፈቻ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እንዳሉት የዛሬ ተማሪዎች የነገዋን ኢትዮጵያ ተረካቢ ትውልድ ናቸው። በአካልና በአዕምሮ ብሩ የሆነ ትውልድ ለሀገር እድገትና ብልጽግና ያለው ሚና ከፍተኛ ስለሆነ ጠንክሮ መስራት፣ ማንበብ፣ መመራመርና ለቤተሰብና ለሀገር አለኝታ መሆን ይገባል ብለዋል። ስፖርት ለጤንነት ብቻ ሳይሆን ለአእምሯዊ ብስለትና እድገት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን ጠቁመው፤ ተማሪዎችም ይህን ተገንዝበው ለተግባራዊነቱ ሊተጉ ይገባል ብለዋል።   ተማሪዎች ማህበራዊ ሚዲያ የሚመራቸው ሳይሆኑ በስነ ምግባር የታነጹና ማህበራዊ ሚዲያውን የሚመሩ መሆን እንደሚገባቸውም ተናግረዋል። ስፖርት ለወዳጅነት፣ ለአንድነትና ለሰላም ፋይዳው የጎላ በመሆኑ በውድድሩ ጠንካራ ፉክክር በማድረግ በስፖርታዊ ጨዋነት ማከናወን ይገባል ብለዋል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጌቱ ነገዎ በበኩላቸው ፤ ከዛሬ ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ሳምንታት በሚቆየው በዚሁ ውድድር በክልሉ የሚገኙ ሁሉም የግልና የመንግስት ትምህርት ቤቶች እንደሚሳተፉ ገልጸዋል።   ውድድሩም በትምህርት ቤቶች ውስጥ ጤናማና ንቁ ትውልድ ለመፍጠር ያለንን ቁርጠኝነት የምናሳይበት ነው ብለዋል። እንዲሁም በተማሪዎችና መምህራን መካከል ያለውን የእርስ በርስ ግንኙነት ለማጠናከር እና ክልል አቀፍ ስፖርተኞችን ለማፍራት ዓላማ አድርጎ መዘጋጀቱን አቶ ጌቱ ገልጸዋል። በውድድሩ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ በክልሉ የሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት ተማሪዎች፣ መምህራንና የስፖርት ባለሙያዎች ተገኝተዋል። ውድድሩ ዛሬ በከተማው በሚገኘው ኢማም አህመድ ስታዲየም ሲጀመር በ100 ሜትር የመምህራን ሩጫ ውድድር አባድር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲያሸንፍ፤ በወረዳ ሴቶች ሸንኮር ወረዳ እንዲሁም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች አሁንም አባድር ሁለተኛ ደረጃ አሸናፊ ሆነዋል።
የጋራ መኖሪያ ቤቶችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል
Apr 17, 2026 69
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ) ፦ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳመለከተው በኮዬ ፈጨ ኮንዶሚኒየም በተለያዩ ሳይቶች የሚገኙ ነዋሪዎችን በተናጠል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በኮዬ ፈጨ ኮንዶሚንየም ፕሮጀክት 11 እና 17 የሚኖሩ ከ12 ሺህ በላይ ነዋሪዎች በየብሎኩ በተገጠመ ባለ ሦስት ፌዝ ቆጣሪ በጋራ ይጠቀሙ እንደነበር አስታውሶ፤ በዚህም በኃይል ማነስና መቆራረጥ ሲቸገሩ ቆይተዋል ብሏል፡፡ አሁን ግን በተናጠል ቆጣሪ እንዲገጠምላቸው በመደረጉ በቂ ኃይል እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል ብሏል በመረጃው፡፡ ነዋሪዎቹን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግም 17 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የዝቅተኛ ቮልቴጅ መስመር፣ የ8 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ ቮልቴጅ የመሬት ውስጥ ተቀባሪ መስመርና የ4 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ ቮልቴጅ የአየር ላይ መስመር ዝርጋታ መከናወኑን ገልጿል። በዚህም 53 ትራንስፎርመሮች መተከላቸውንና ለነዋሪዎቹ 12 ሺህ 100 ቆጣሪዎች መገጠማቸውንም አረጋግጧል። በቀጣይ በአዲስ አበባ ቤቶች በኩል የሚፈፀሙ ክፍያዎች እንደተጠናቀቁ በኮዬ ፈጨ ኮንዶሚኒየም በተለያዩ ሳይቶች የሚገኙ ነዋሪዎችን በተናጠል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የማድረግ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አመላክቷል። አገልግሎቱ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ለማሳደግ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እየሰራ እንደሚገኝም አስታውቋል። Ethiopian News Agency #ኢዜአ
በክልሉ የፍትህ ስርዓቱን ፈጣን፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ በማድረግ ረገድ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ናቸው
Apr 16, 2026 264
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የፍትህ ስርዓቱን ፈጣን፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ በማድረግ ረገድ የተጀመሩ ስራዎች የሚበረታቱ መሆኑን የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ገለጸ። ‎የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ስራ አስፈፃሚ አባላትና አመራሮች የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የስራ ክንውንና አጠቃላይ የሪፎርም ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።   ‎በዚሁ ጊዜ አስተያየታቸውን የሰጡት ‎የማህበሩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ህብረት አቡሃይ፤ በክልሉ የፍትህ ስርአቱን በማሻሻልና ተግባራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን አይተናል ብለዋል። የሪፎርም ስራው ጅምር ትልቅ ለውጥ የታየበት መሆኑን አንስተው እስከ ታች በማውረድ የዜጎችን የፍትህ ፍላጎትና ተደራሽነት ማስፋት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የፍትህ ስርዓቱን ፈጣን፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ በማድረግ ረገድ የተጀመሩ ስራዎች የሚበረታቱ መሆኑን አንስተው በተለይም የሴቶችና ህፃናት የፍትህ አገልግሎት በልዩ ትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። በዘርፉ አገልግሎት አሰጣጥ የተመዘገቡ ስኬቶችን ማስቀጠሉ እንዳለ ሆኖ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ይበልጥ መስራት እንደሚገባም አንስተዋል።   የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉዓለም ቢያዝን፤ የፍትህ ስርዓቱ ሪፎርም አገልግሎቱን ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ ማድረግ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ የባህል ፍርድ ቤቶች በህግ ዕውቅና አግኝተው ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸው በሁሉም ረገድ ዜጎች ፈጣንና ሚዛናዊ የፍትህ አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም በሪፎርሙ የሚታዩ ለውጦችና ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።
ኢኮኖሚ
በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር የክላስተር የፍራፍሬ ልማት ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተከናወነ
Apr 17, 2026 25
ደዋጨፋ፤ሚያዝያ 9/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደና በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የሚመራ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ በክላስተር የሚካሄድ የፍራፍሬ ልማት ችግኝ ተከላ አስጀምሯል። ከርዕሳነ መስተዳድሮቹ በተጨማሪ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ፣እንዲሁም በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር)ና ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ተገኝተዋል።   በተጨማሪም ሌሎች የክልል፣የዞን አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመርሃ ግብሩ ታድመዋል። በክልሉ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፣የዞኑ ስነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ለፍራፍሬ ልማት ምቹ ነው። ዞኑ በገፅና በከርሰ ምድር ውሃ የታደለ በመሆኑ ያለውን ጸጋ በመጠቀም የኩታ-ገጠም የፍራፍሬ ልማት ስራን በዛሬው እለት በይፋ መጀመሩን ገልጸዋል።   ይህም እስካሁን በተበጣጠሰ መልኩ ሲካሔድ የነበረውን የፍራፍሬ ልማት ወደ ኩታ ገጠም በማስፋት ለአገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ታልሞ እየተሰራ መሆኑን ያመላክታል ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም የአካባቢው አርሶ አደሮችን በማደራጀትና ግንዛቤ በመፍጠር የፍራፍሬ ልማት ስራ አዋጭ መሆኑን ከግንዛቤ አስገብተው ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በቡና ክላስተር የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ሊጠናከሩ ይገባል
Apr 17, 2026 47
አረካ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቡናን በክላስተር በማልማት የአርሶ አደሮችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመረው ተግባር መጠናከር እንዳለበት የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ ገብረመስቀል ጫላ ተናገሩ። ቡናን በክላስተር ማልማት ላይ ያተኮረ ክልላዊ የቡና ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዛሬ በወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ አቹራ ቀበሌ ተካሂዷል።   "የቡና ምርት ዕድገት ለኢኮኖሚያችን" በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደ የችግኝ ተከላ መርሀግብር ላይ ‎የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንደገለጹት፤ በመንግስት ትኩረት ከተሰጣቸው ብዝሃ የኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል ግብርና አንዱ ነው። ከግብርና ምርቶች መካከል ቡና የአንበሳውን ድርሻ እንደሚይዝ ጠቅሰው፣ ቡናን በክላስተር ለማልማት የተጀመረው ሥራ ልማቱን ከማዘመን ባለፈ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በእጥፍ ስለሚያሳድገው መጠናከር አለበት ብለዋል። ‎የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በማስፋፋትና የግብርና ስራውን በማዘመን ለምርታማነት መጨመር ሁሉም በተለይ የዘርፉ አመራር መረባረብ አለበት ሲሉም አስገንዝበዋል።   ህብረተሰቡ ውሃ ገብ ከሆኑ አካባቢዎች ባህር ዛፍና ያረጁ ቡናዎችን በመንቀልና በመጎንደል የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ እንዲሆን የባለሙያዎች ድጋፍ መጠናከር እንዳለበትም አሳስበዋል። ‎በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ ‎የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቡና ላይ መስራት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚኖረው አስተዋጽኦ የጎላ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል።   ለዚህም ‎ዘንድሮ በክልል አቀፍ ደረጃ ከ40 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኞች እንደሚተከሉ ጠቅሰው፣ በቡና ከሚለማው መሬትም 5 ሺህ ሄክታሩ በኩታ ገጠም እንደሚለማ አመልክተዋል። በክልሉ በባህር ዛፍ የተሸፈኑ ማሳዎችን በተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች የመቀየር ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ያሉት ኃላፊው ዘንድሮ ከሚተከሉ የቡና ችግኞች መካከል 34 ሚሊዮን የሚሆነው በተያዘው ሚያዚያ ወር የሚተከል ነው ብለዋል። ‎‎የቡና ልማቱ የአርሶ አደሩን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለብዙዎች የሥራ ዕድል እየፈጠረ ነው ያሉት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሠማ (ረ/ፕሮፌሰር) ናቸው። ‎ይህንን ለማጠናከር ለዘንድሮ የበልግ ወቅት ከ6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ዝግጅት፣ የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ፣ የኮምፖስት እና የጥላ ዛፎች ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።   ‎ከዚህ በተጨማሪ በዞኑ በልዩ ንቅናቄ 2ሺህ 253 ሄክታር የነባር ቡና ማሳ ዕድሳት ሥራ እና ከ2 ሺህ በላይ ሄክታር አዲስ የቡና ማሳ ዝግጅት ተከናውኗል ብለዋል። ‎‎በዞኑ በተለያዩ ክላስተሮች 1 ሺህ 207 ሄክታር ማሳ ላይ በኩታ ገጠም ቡና ተክሎ ለማልማት ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ ወደ ትግበራ መገባቱንም ጠቁመዋል። በዛሬው የተከላ መርሃ ግብር ከተሳተፉት ነዋሪዎች መካከል አቶ ዘለቀ ስኔቦ እና መጋቤ ተስፋዬ ሹኬ፤ ከዚህ ቀደም ቡናን በባህላዊ መንገድ ስለሚያመርቱ ከልማቱ ብዙም ተጠቃሚ እንዳልነበሩ አስታውሰዋል። ከዘርፉ ባለሙያዎች በተሰጣቸው ትምህርት መሰረት የባህር ዛፍ ቦታን በተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች በመተካታቸው የተሻለ ምርት ማግኘት መጀመራቸውን ተናግረዋል። በተለይ ቡናን በክላስተር ማልማት ድካምንና ያለአግባብ ይባክን የነበረን ጊዜ በመቀነስ ተጠቃሚነትን ስለሚያሳድግ አጠናክረው ለማስቀጠል መዘጋጀታቸውን ነው የገለጹት። በቡና ችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ ከክልል ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ሥራ ኃላፊዎችና የወረዳው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በጎንደር ከተማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 11 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ገብተዋል
Apr 17, 2026 61
ጎንደር ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በጎንደር ከተማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 11 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ። በከተማው በ400 ሚሊዮን ብር ወጪ በአንድ ባለሀብት የተገነባ የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ተመርቆ ስራ ጀምሯል። የመምሪያው ሃላፊ ግርማይ ልጃለም እንዳሉት፤ በዘንድሮው ዓመት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 20 መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ምርት ማምረት ለማሸጋገር እየተሰራ ነው። ባለፋት ዘጠኝ ወራት በተደረገ የተቀናጀ ጥረትም 10 መካከለኛና አንድ ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪ ወደ ማምረት እንዲገቡ መደረጉን ገልጸዋል። ወደ ምርት እንዲገቡ የተደረጉት ኢንዱስትሪዎችም በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ማምረት ላይ የተሰማሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ከ500 በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የስራ ዕድል በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማሳደግ ያስቻሉ ሲሆን ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ እንደሆኑም ገልጸዋል።   አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ወደ ማምረት መሸጋገራቸውም ገበያን በማረጋጋት፣ ተኪ ምርቶችን በማምረትና የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንም አመልክተዋል። በከተማው የሰፈነው ሠላም አምራች ኢንዱስትሪዎቹ በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ እንዲገቡ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ያሉት ደግሞ የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው።   የከተማ አስተዳደሩ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የግንባታ መሬት ከማዘጋጀት ጀምሮ መሠረተ ልማቶችን በማሟላት ፈጥነው ወደ ስራ እንዲገቡ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል። የዘይት ፋብሪካው ባለቤት አቶ አደራጀው ገብረሚካኤል በበኩላቸው፤ ፋብሪካው በቀን 20 ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት የማምረት አቅም እንዳለው ተናግረዋል።   ፋብሪካው በቀን 400 ኩንታል አኩሪ አተር በጥሬ እቃነት የሚጠቀም ሲሆን ይህም በግብርና ስራ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች አስተማማኝ የገበያ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ለ30 ወገኖች የስራ እድል መፍጠሩን ጠቅሰው፤ 400 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ ከተማ አስተዳደሩ ባመቻቸው 7 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ መገንባቱንም ጠቁመዋል። በስነ ስርዓቱ ላይም የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የማይበገር የምግብ ስርዓት እየገነባች ነው
Apr 17, 2026 78
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ያሏትን የተፈጥሮ ሀብቶች በሚገባ በማወቅና በማልማት ለዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የማይበገር የምግብ ስርዓት እየገነባች መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ። ላለፉት ጥቂት ዓመታት መንግሥት ተግባራዊ ባደረገው የባለብዙ ዘርፍ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠቱ፣ ዘርፉ አስደናቂ የምርት እድገትና መዋቅራዊ ሽግግር እያስመዘገበ ይገኛል። በተለይም በበጋ ስንዴ እና በመስኖ ልማት ረገድ በስፋት የተከናወኑት ተግባራት ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የስንዴ አምራች ሀገር እንድትሆን ያስቻሉ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ አፋጥኖታል። ይህ ስኬት ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የኢኮኖሚ ጥንካሬዋን እና የግብርና ምርታማነት አቅሟን በተግባር ያሳየ ሆኗል። የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት በተሟላ መልኩ ለማረጋገጥ የምርትና ምርታማነት እድገት መሰረታዊ ነው። ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ስንዴ ከውጭ ገዝታ ለማስገባት ታወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጪ ማስቀረት መቻሏን ገልጸዋል። መንግሥት የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመንና ምርትን ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት፣ በግዥ ከውጭ ይገባ የነበረውን ስንዴ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መተካት እንደተቻለ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። ይህ ታሪካዊ ስኬት የሀገሪቷን የውጭ ምንዛሬ ከመታደጉ ባለፈ ራስን በምግብ ለመቻል ለተያዘው ብሄራዊ ግብ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በምርምር፣ በግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና በተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም ረገድ ሰፊ ስራዎችን በማከናወን ላይ ትገኛለች ብለዋል። በተለይም የማዳበሪያ አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት የተጀመረው የፋብሪካ ግንባታ ተጠናቆ ወደ ስራ ሲገባ ከፍተኛ የኢኮኖሚ እና የምርታማነት ለውጥ እንደሚያመጣ ገልጸዋል። ምርታማነታቸው ከፍተኛ የሆነና በሽታን የመቋቋም አቅም ያላቸው ምርጥ ዘሮች በራስ የምርምር አቅም ማውጣት የሚያስችል የግብርና ምርምር ስርዓት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያላትን የመሬት፣የውሃ እና የሰው ሃይል አቅም በማቀናጀት ለግብርናው ዘርፍ የሚያስፈልጉ የሃይል እና የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ለማሟላት የምታደርገው ጥረት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ነው ያስገነዘቡት። አንድ ሀገር በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከሰቱ የጂኦፖለቲካ ለውጦች በነዳጅ አቅርቦትና በምግብ ሉዓላዊነት ላይ የሚያስከትሉትን ብርቱ ተጽዕኖ ለመቋቋም የሚያስችል ስራ በትኩረት መከናወን እንዳለበት አንስተዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋዎች በሚገባ ለይታ በማወቅና በማልማት፣ ማንኛውንም ወቅታዊ ዓለም አቀፍ ቀውስ መቋቋም የምትችል ጠንካራ ሀገር ለመገንባት በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ይህም ከውጭ የሚመጡ ተጽዕኖዎችን ተቋቁማ የምግብ ሉዓላዊነቷን በተገቢው መንገድ እንድታረጋግጥ የሚያስችላት መሆኑንም ገልጸዋል። የምግብ ሉዓላዊነቷን ያረጋገጠች ጠንካራ ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው ጥረት አርሶና አርብቶ አደሮች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉም ብለዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሰራተኞችን የስራ ባህል አሻሽሏል
Apr 17, 2026 97
አዳማ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የሰራተኞችን የስራ ባህል ማሻሻሉን የአገልግሎቱ ስራ አስኪያጅ ገለጹ። የአዳማ ከተማ አስተዳደር የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ መኩሪያ ድንቁ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማው 138 አገልግሎቶች በመሶብ አንድ ማዕከል ውስጥ እየተሰጡ ነው። በዚህም 31 የሚሆኑ የአስተዳደሩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን በአንድ ማዕከል በማሰባሰብ የተቀናጀ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል። በማዕከሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የተቀናጀ ፈጣን አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ እየተቻለ መሆኑን ጠቁመው፤ ለተገልጋዮችም ምቹና ፅዱ በሆነ አካባቢ አገልግሎት ማግኘት ማስቻሉን ተናግረዋል። የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩ የሰራተኞችን የስራ ባህል ከመለወጡም ባለፈ የመንግስት የስራ ሰዓትን በአግባቡ የመጠቀም ዝንባሌ እየጨመረ መምጣቱንም ገልጸዋል። በማዕከሉ 18 የሚሆኑ የለሙ ቴክኖሎጂዎች በተሟላ መልኩ የኦንላይን አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የገለጹት ሃላፊው፤ የህዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሠራተኞችን አቅም በቴክኖሎጂ የማብቃት ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በከተማዋ ደረጃ ካለው ማዕከል ባለፈ በዳቤ፣ በአባ ገዳና በቦሌ ክፍለ ከተሞች የአንድ ማዕከል አገልግሎቱን ማስፋፋት ተችሏል ብለዋል። በአዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሲገለገሉ ያገኘናቸው አቶ አብረሃም ወይሴ፤ ለመሬት ጉዳይ አገልግሎት ለማግኘት ፈልገው መምጣታቸውን ገልጸዋል።   የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ከመጀመሩ በፊት ችግሮች እንደነበሩ አንስተው፤ በተለይ ከአንድ መስሪያ ቤት ወደ ሌላው የሚደረገው ጉዞ እና ምልልስ ፈታኝ እንደነበር ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት ሁሉንም አገልግሎት በአንድ መስኮት እያገኘን ነው ሲሉ ገልጸዋል። ወይዘሮ አለምነሽ ሽብሩ በበኩላቸው "ከበር ጀምሮ ያለው አቀባበልና ማስተናገጃው በጣም ደስ የሚል ነው" በማለት ይገልጻሉ።   በምቹ ማዕከል የተቀላጠፈ አገልግሎት በማግኘታቸው መደሰታቸውንም ተገልጋዮቹ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ያላትን ልምድ ለአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አጋራች
Apr 16, 2026 927
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ ያካበተችውን ተጨባጭ ልምድ ለአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አባላት አጋርታለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የመሩትን የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት የሚኒስትሮች ስብሰባን አስመልክቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት የሊቀ መንበርነት ሚናዋን በብቃት እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል።   ዛሬ በበይነ-መረብ በተካሄደው በዚህ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ተሞክሮ ለማጋራት አመቺ ዕድል መፈጠሩን ቃል አቀባዩ አንስተዋል። ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለኢኮኖሚ፣ ለአስተዳደር እንዲሁም ለሰላምና ፀጥታ ሥራ ያለውን የጎላ ፋይዳ ለሚኒስትሮቹ አስገንዝበዋል ብለዋል። በተለይም ቴክኖሎጂው ግጭቶችን በመከላከል፣ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን በማስተላለፍ እና የሰላም ሂደቶችን በመደገፍ ረገድ ያለውን አበርክቶ አብራርተዋል። አምባሳደር ነብያት አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቅንጦት ሳይሆን ጠቃሚ የልማት መሣሪያ መሆኑን ኢትዮጵያ ተገንዝባለች ብለዋል። በዚህ ዘርፍም የተቀናጁ ተቋማትን በማቋቋም ህዝቡ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ቀልጣፋ ዲጂታል አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተሞክሮ እና በአቅም ግንባታ ረገድ እየተከናወነ ያለውን የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ በአብነት ለመድረኩ መቅረቡን ተናግረዋል። በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሻምፒዮን ሆነው መመረጣቸው፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ተሞክሮ ለሌሎች ሀገራት እንድታካፍል ትልቅ ዕድል መፍጠሩን አምባሳደሩ ገልጸዋል። አፍሪካ በቀደመው የኢንተርኔት ዘመን ዘግይታ መግባቷን ያስታወሱት ቃል አቀባዩ፤ አሁን ግን አህጉሪቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘመን ተገቢውን ቦታ በመያዝ የመሪነት ሚና እንዲኖራት ኢትዮጵያ ያላትን ጽኑ አቋም በመድረኩ ማንጸባረቋን ገልጸዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ግብ ለማሳካት የዲጂታል አስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል
Apr 16, 2026 186
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ግብ ለማሳካት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክህሎትና የዲጂታል አስተሳሰብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በለጠ እሱባለው ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ከአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ጋር በመተባበር "አመራር በሰው ሰራሽ አስተውሎት" በሚል መሪ ሃሳብ ሴሚናር አዘጋጅቷል፡፡   የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በለጠ እሱባለው በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን መገልገል ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ሆኗል፡፡ ዘመኑ የሚጠይቀውን አመራር ለመስጠት በዘርፉ ራስን ማዘጋጀት እንደሚገባ ገልጸው፤ እንደ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ያሉ ተቋማት ደግሞ ሥራቸው ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር የተያያዘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ፓርኩ በዘርፉ ልምድና አቅም ያላቸው ባለሙያዎችን በማምጣት የተቋሙን ሰራተኞችና የሥራ ሀላፊዎች ሰው ሰራሽ አስተውሎትን እንዴት መጠቀም እንዳለባቸው ግንዛቤ እንዲፈጠርላቸው እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወን የተቋሙን ግብ ለማሳካት የሰው ሰራሽ አስተውሎትን መሰረት ያደረገ ጥረት መኖሩንም ተናግረዋል፡፡ የዲጂታል ኢትዮጵያን 2030 ስትራቴጂ ግብ ለማሳካት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክህሎትና የዲጂታል አስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት ይገባል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ቦርድ ሊቀ መንበርና የአፍሪካ ቴክኖሎጂ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ባህሩ ዘይኑ፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡   ኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ በመረዳት የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አቋቁማለች ብለዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ /ኤ.አይ/ ዩኒቨርሲቲ ለመክፈት በሂደት ላይ መሆኗን አስታውሰዋል፡፡ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ገዥና ተቀባይ እንደነበረች አስታውሰው፤ ፖሊሲ በማዘጋጀት የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት በመዘርጋት ቴክኖሎጂ ሰጭና ለሌሎች ሀገራት አቅራቢ ወደ መሆን ደረጃ ተሸጋግራለች ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ተባባሪ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፕሮፌሰር ሸጋው አናጋው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በሁሉም ዘርፎች ለውጥ እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   ሰው ሰራሽ አስተውሎት የአሰራር ለውጥ መፍጠሩን የጠቀሱት ፕሮፌሰር ሸጋው፤ የተቋማት መሪዎች በቀደመው መንገድ መምራት አይችሉም ብለዋል፡፡ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን ውጤት በሚያመጣ መንገድ ለመጠቀም የተቋማት መሪዎችን በቴክኖሎጂ ማብቃት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የዲጂታል ሽግግር ለማምጣት የአስተሳሰብና የባህል ለውጥ እንደሚያስፈልግ ገልጸው፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕውቀትና ክህሎት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል፡፡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘመን ሁኔታዎችን አስቀድሞ በመተንበይ ለውጥ በሚያመጡ ጉዳዮች ላይ አመራር ለመስጠት ክህሎት፣ ሥነ ምግባርና ሽግግር መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡   በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰላምይሁን አደፍርስ በበኩላቸው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የመሪነት ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ መንግሥት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ፖሊሲ በማውጣት ዘርፉን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በፍጥነት እያደገ ያለ ዘርፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዘርፉን እድገት የሚመጥን የመንግስት ቁርጠኝነት መኖሩን ገልጸዋል፡፡
የሰው ሰራሽ አስተውሎት የጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞችን ስራ በመደገፍ ረገድ ከፍተኛ ለውጥ እያመጣ ነው
Apr 16, 2026 172
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞችን ስራ በመደገፍ ረገድ ከፍተኛ ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የጤና ሚኒስቴር በሰው ሰራሽ አስተውሎት (Al) በመደገፍ ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የስራ አጋዥ ተግባራትን በማጎልበት በተመረጡ ወረዳዎች በተደረገው የሙከራ ትግበራ ማስተዋወቅ እና እስካሁን ያለውን ሂደት የሚገመግም መድረክ አካሂዷል።   በጤና ሚኒስቴር የማህበረሰብ ተሳትፎና የመጀመርያ ደረጃ ጤና ክብካቤ መሪ ሥራ አስፈፃሚ እስራኤል አታሮ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ሚኒስቴሩ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በመጠቀም የተሻለ የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። በዲጂታል ቴክኖሎጂ መረጃ አያያዝ ማጠናቀር እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ ህክምና አሰጣጥ ስራዎችን ማከናወን የዚሁ አካል መሆናቸውን አመልክተዋል። የትግበራ ምዕራፍ ላይ የምትገኘው 'ሀዋ' የተሰኘችው የሰው ሰራሽ አስተውሎት የጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞችን ስራ በመደገፍ ረገድ ትልቅ ለውጥ ማምጣት ታስችላለች ብለዋል። ይህ አዲስ አሰራር ባለሙያዎች በታብሌት በመታገዝ አዳዲስ የበሽታ ምልክቶችን በፍጥነት እንዲለዩና የወረቀት ፓኬጆችን ወደ ዲጂታል በመቀየር መረጃን በቀላሉ እንዲያስተዳድሩ ያግዛል ብለዋል።   በሰው ሰራሽ አስተውሎት (Al) የተደገፈ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥን ለማጠናከር ካሁን ቀደም ተግባራዊ ከተደረገባቸው ወረዳዎች በተጨማሪ ተደራሽ ባልተደረገባቸው አካባቢዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። ይህ ቴክኖሎጂ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች መደበኛ ሥራቸው ላይ የተሻለ እገዛ በማድረግ ውጤታማ አገልግሎት እንዲሰጡ ያስችላል ነው ያሉት፡፡ የኤክስቴንሽን ባለሙያዎች መረጃን በዲጂታል እንዲይዙና አዳዲስ የበሽታ ምልክቶችን ለይተው ለቀጣይ ህክምና ማስተላለፍ እንደሚያስችል ተጠቅሷል። እንዲሁም ከጤና ኬላዎች ወደ ጤና ጣቢያዎች የሚደረገውን አላስፈላጊ ሪፈራልና የታካሚዎች እንግልት ለመቀነስና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (Al) ታካሚዎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ የጤና ኬላዎች አፋጣኝ ህክምናና እፎይታ እንዲያገኙ ያስችላል ተብሏል። በ'ላስት ማይል ኸልዝ' ከፍተኛ የፕሮግራም ሥራ አስኪያጅ ሩት ድሪባ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የጤና ኤክስቴንሽን አጋዥ የሰው ሠራሽ አስተውሎት መርጃው ለአንድ ዓመት ተኩል ያህል በሙከራ ደረጃ መቆየቱን ተናግረዋል።   ሰው ሰራሽ አስተውሎት የጤናውን ዘርፍ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልፀው፤ በተጨማሪም እንደሃገር የተያዘውን ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን እውን ለማድረግ ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የቀሪ ሳምንታት መርሐ ግብር ይፋ ሆነ
Apr 17, 2026 52
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር የ2018 የውድድር ዘመን መጠናቀቂያ የሆኑትን ከ29ኛ እስከ 38ኛ ሳምንት ያሉ የጨዋታ መርሐ ግብሮችን ይፋ አድርጓል። እንደ አክሲዮን ማህበሩ መግለጫ ከሆነ፣ የሊጉ ውድድር የሚቀጥለው የኢትዮጵያ ዋንጫ ጨዋታዎች ከተከናወኑ በኋላ ሲሆን፣ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ዳግም እንደሚጀመር ታውቋል።   ይህ የቀሪ አሥር ሳምንታት መርሃ ግብር የሊጉን ሙሉ የውድድር ጉዞ የሚያጠቃልል ነው። የቀሩት ሳምንታት ጨዋታዎች በሁለት የሀገሪቱ ስታዲየሞች እንደሚከናወኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ጨዋታዎቹም በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየምና በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳሉ።   የኢትዮጵያ ዋንጫ የጨዋታ ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ የ33ኛ እና የ34ኛ ሳምንት መርሃ ግብሮች ላይ ማሻሻያ ሊደረግ እንደሚችል ማህበሩ አመልክቷል። በተጨማሪም፣ የውድድር ዘመኑ ማጠቃለያ የሆኑት የ37ኛ እና የ38ኛ ሳምንት ጨዋታዎች የክለቦችን የደረጃ እና የውጤት ፉክክር መሰረት በማድረግ ለውጥ ሊደረግባቸው እንደሚችልም ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ለማጠናቀቅ ከቱርኪዬ ጋር ዛሬ ትጫወታለች
Apr 17, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ያዘጋጀው የ"UEFA Frendship Cup" ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ውድድር ዛሬ ይጠናቀቃል። ውድድሩ በቱርኪዬ ከመጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ሲካሄድ ቆይቷል። በወዳጅነት ዋንጫው ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ስምንት ሀገራት ተሳትፈዋል። የኢትዮጵያ ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ለማጠናቀቅ ከቱርኪዬ ጋር ዛሬ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ትጫወታለች። በምድብ ሁለት ጨዋታዋን ያደረገችው ኢትዮጵያ በምድቧ ሶስት ጨዋታዎችን አድርጋ ሁለቱን ስታሸንፍ አንድ ጊዜ አቻ ወጥተዋል። በስድስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በምድብ አንድ የተደለደለችው ቱርኪዬ በስድስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። በአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር የውድድር ደንብ መሰረት ከየምድቡ ሁለተኛ የወጡ ሀገራት ሶስተኛ ደረጃን ለማግኘት ይጫወታሉ። ከጨዋታው በፊት ብሔራዊ ቡድኑ የመጨረሻ ልምምዱን ትናንት ማከናወኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በአሰልጣኝ ቻለው ለሜቻ የሚመራው ቡድን በውድድሩ ላይ ጥሩ እንቅስቃሴ አድርጓል። ብሔራዊ ቡድኑ መልካም ጉዞውን ለማሳመር ከቱርኪዬ ጋር ለደረጃ ይጫወታል። ከየምድቡ አንደኛ የወጡት ፓራጓይ እና ኖርዌይ ዋንጫውን ለማንሳት ዛሬ ይጫወታሉ። ኢትዮጵያ፣ ኮስታሪካ፣ ዩራጓይ፣ ኖርዌይ፣ ቱርኪዬ፣ ፓራጓይ፣ ሞሮኮ እና ኡዝቤኪስታን በውድድሩ ላይ የተሳተፉ ሀገራት ናቸው። የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ያዘጋጀው የወዳጅነት ዋንጫ ከውድድር ባለፈ የክፍለ አህጉራዊ እግር ኳስ ልማት ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። በተጨማሪም የእርስ በእርስ የልምምድ ልውውጥ የተደረገ ሲሆን የተለያዩ ስልጠናዎች እና ጉብኝቶችም የውድድሩ አካል ነበሩ።
በያዝነው ወር ሶስት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ኩነቶች አዲስ አበባ ይካሄዳሉ
Apr 16, 2026 182
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 8/2018(ኢዜአ)፦ዓለም አቀፉ አዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የአትሌቲክስ ውድድርን ጨምሮ አዲስ አበባ ውስጥ በሚያዚያ ወር ሶስት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ኩነቶች ይካሄዳሉ። ከሚካሄዱት ዓለምአቀፍ ስፖርታዊ ኩነቶች ውስጥ አንዱ የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የአንድ ቀን የአትሌቲክስ ውድድር በመጪው ቅዳሜ ይካሄዳል። ይህ ውድድር በአዲስ አበባ ሲካሄድ የመጀመሪያው ሲሆን መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የስፖርት መሰረተ ልማቶች መስፋፋት ምቹ ሆኔታ መፍጠሩ ነው የተገለፀው።   በአዲስ አበባ ስታዲዮም በሚካሄደው ውድድር ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ እና ብዙ ተከታይ ያላቸው አትሌቶች ይሳተፉበታል ተብሏል። ሲቲ ማውንቴን ባይክ ኢሊሚኔተር ዓለም አቀፍ የብስክሌት ውድድር እና ግራንድ ኢትዮጵያን ረን ሚያዝያ ውስጥ የሚካሄዱ ውድድሮች ናቸው። ከተማ አስተዳደሩ ውድድሩን ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቂ ዝግጅቶች ከማድረግ በዘለለ በኢትዮጵያ ያሉትን የስፖርት መሰረተ ልማቶች ለማስተዋወቅ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ተመልክቷል።
ባየር ሙኒክ እና አርሰናል ለግማሽ ፍጻሜ አለፉ
Apr 16, 2026 255
አዲስን አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ቀሪ ሁለት የሩብ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታዎች ማምሻውን ተደርገዋል።   በአሊያንዝ አሬና ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በመደበኛው ክፍለ ጊዜ ባየር ሙኒክ ሪያል ማድሪድን 4 ለ 3 አሸንፏል። አሌክሳንደር ፓቭሎቪች፣ ሃሪ ኬን፣ሉዊስ ዲያዝ እና ማይክል ኦሊሴ ለባየር ሙኒክ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። አርዳ ጉለር ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ኪሊያን ምባፔ ቀሪዋን ጎል ለማድሪድ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ተቀይሮ የገባው ኤድዋርዶ ካማቪንጋ በ86ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ወጥቷል። ከቀይ ካርዱ በኋላ ሙኒክ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል። በጨዋታው ባለሜዳው ባየር ሙኒክ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ቢወስድም ሪያል ማድሪድ በመልሶ ማጥቃት የተሻሉ የግብ እድሎች ፈጥሯል። ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ አርዳ ጉለር ዳኛ በመናገሩ በቀይ ካርድ ወጥቷል። ባየር ሙኒክ በድምር ውጤት 6 ለ 4 በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜ አልፏል። በሌላኛው መርሐ ግብር አርሰናል እና ስፖርቲንግ ሊዝበን ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።   በኤምሬትስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በቂ የግብ እድሎች የተፈጠሩበት አልነበረም። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በድምር ውጤት 1 ለ ዐ በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ተጠናቋል። በግማሽ ፍጻሜው ባየር ሙኒክ ከፒኤስጂ የሚያደርጉት ጨዋታ ከወዲሁ በጉጉት ይጠበቃል።   አርሰናል በግማሽ ፍጻሜው ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ይገናኛል። የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች በሚያዚያ ወር መጨረሻ ይደረጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በክልሉ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዝግጅት ላይ ከሚገኙ ችግኞች መካከል 70 በመቶው የፍራፍሬ ችግኞች ናቸው 
Apr 17, 2026 51
በጋምቤላ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ልማት እየተዘጋጁ ከሚገኙት ችግኞች መካከል 70 ከመቶ የሚሆኑት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡ በክልሉ ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በ70 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ እንደሆነ ቢሮው ገልጿል። በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ ኬት ቾል ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚያግዙና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ላላቸው ችግኞች ትኩረት ተሰጥቷል።   በዚህም 70 በሚሆኑ የግልና የመንግስት የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች እየተዘጋጁ ከሚገኙት ችግኞች መካከል 70 ከመቶ የሚሆኑት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን ተናግረዋል። ከችግኞቹ መካከል ማንጎ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ ፣ ዘይቱናና ሎሚ ዋነኞቹ እንደሆኑም ገልጸዋል። ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ልማት እየተዘጋጁ ካሉት የፍራፍሬ ችግኞች ባለፈ ከአካባቢው የአየር ንብረት ጋር የሚጣጣሙ የደን ችግኞች እየተዘጋጁ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በበጋው ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የተከናወነባቸው ከዘጠኝ ሺህ ሄክታር በላይ የተራቆቱ አካባቢዎችን ስነ-ህይወት ለማልበስ የመረጣና የቦታ ልየታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።   በክልሉ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የተተከሉት የፍራፍሬና ሌሎች ችግኞች የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ከመቀየር ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ረገድ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙም ተናግረዋል። በቀጣይም በክረምቱ ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በሚያግዙ ችግኞች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
በክልሉ የህብረተሰቡ ችግኝ የመትከል ባህል እያደገ መጥቷል
Apr 16, 2026 130
ዋጂፎ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡ ችግኝ የመትከል ባህል እያደገ መምጣቱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጹ። በክልሉ ጋሞ ዞን የ2018 ዓ.ም የበልግ ወቅት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር "አረንጓዴ አሻራ ለተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በምዕራብ አባያ ወረዳ ዋጂፎ ከተማ ተካሂዷል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በአየር ንብረት ለውጥ የሚከሰተውን የተፈጥሮ አደጋ በዘላቂነት ለመቋቋም ለችግኝ ተከላ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል። የለውጡ መንግስት በአየር ንብረት ለውጥ የሚከሰትን ችግር መቋቋም እንዲቻል ለአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተተከሉ ችግኞች የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እያገዙ መሆኑን ጠቀመው፣ በክልሉ ህብረተሰቡ ችግኝ የመትከልና አካባቢውን የመንከባከብ ሥራ ባህሉ እያደረገ መምጣቱን ተናግረዋል።   የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አደጋ ለመከላከል ችግኝ ተከላን የዘወትር ተግባር ማድረግ እንደሚገባ ያሳሰቡት አበባየሁ (ዶ/ር)፣ ችግኝ ተከላው ለግብርና ምርታማነት፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ገቢን ለማሳደግ እያገዘ መሆኑን አስረድተዋል። ልማትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የሚከናወነውን የልማት ሥራ ማጠናከር ይገባል ያሉት ደግሞ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊና የዲላ ክላስተር አስተባባሪ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ናቸው።   መርሀ ግብሩ ለምግብ ዋስትና፣ ለዘላቂ ልማት፣ ለኢንዱስትሪ ሽግግር እንዲሁም ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ የማይተካ ሚና ይጫወታል ብለዋል። በመሆኑም ዘንድሮ በክልሉ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ የጠቀሱት መሪሁን (ዶ/ር)፣ ግብርናን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማረጋገጥ እንደሚሰራም ተናግረዋል። የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በዜጎች ሕይወት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል።   በዘንድሮ የበልግ ወቅት በሚከናወን የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ከዘጠኝ ሚሊዮን በላይ የፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ወደ ትግበራ መገባቱን አንስተዋል። በተለይ በዞኑ በተደጋጋሚ የሚከሰቱ የጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት አደጋዎች ተፈጥሮን በአግባቡ ባለመንከባከብ የሚከሰቱ መሆናቸውን ጠቁመው፣ ለችግኝ ተከላው ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።   በምዕራብ አባያ ወረዳ የዋጂፎ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ሃምሳ አለቃ ዋጋሶ ኦቼ እና አቶ ዳንኤል ዳንጋሮ በበኩላቸው ቀደም ሲል በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የተተከሉ ችግኞች በአካባቢያቸው ተጨባጭ ውጤት ማምጣታቸውን ተናግረዋል። በየዓመቱ በተተከሉ ችግኞች ቀደም ሲል ሞቃት የነበረው የአካባቢው የዓየር ጸባይ እየተስተካከለ መምጣቱን የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ በግብርና ሥራም ተጨባጭ ውጤት እየታየ መሆኑን ተናግረዋል። ለዚህም በመርሀ ግብሩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ፍራፍሬዎች በማልማት ተጨማሪ ገቢ ከማግኘት ባለፈ፣ ለጓሮ አትክልትና ለእንስሳት መኖ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ይህን ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ በዛሬው የችግኝ ተከላ መርሀግብር መሳተፋቸውን ገልጸው፣ በቀጣይም በችግኝ ተከላና እንክብካቤ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የከተማ አስተዳደር የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በሶማሌ ክልል ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የችግኝ ዝግጅት እየተደረገ ነው
Apr 16, 2026 122
ጅግጅጋ፣ ሚያዝያ 8/2018(ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የችግኝ ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡ በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የተተከሉ ችግኞች የአካባቢን ስነምህዳር ከመቀየር ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ በመስጠት ላይ መሆናቸው ይታወቃል። በሶማሌ ክልል አከባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አስተዳደር ቢሮ የደን ልማት ዳይሬክተር ሂቦ ኑር ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በለውጡ ዓመታት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በተከናወኑት የችግኝ ተከላ ተግባራት መሬት መራቆትና የአፈር መሸርሸርን መከላከል እየተቻለ ነው። በክልሉ በመርሃ ግብሩ የተተከሉት ችግኞች የአፈር መሸርሸርና የመሬት መራቆት በመከላከልና የአየር ንብረት ተጽዕኖ ለመቋቋም አበረታች ለውጥ ያመጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም በክልሉ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ለመትከል ታቅዶ የችግኝ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ የታቀደውን የችግኝ ተከላ መርሃግብር ለማሳካት በ160 የግልና የመንግስት ችግኝ ጣቢያዎች ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ችግኞቹ ለማህበረሰቡ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን የሚሰጡ፣ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ዓይነቶች፣ ለደንነት የሚውሉ፣ ለውበትና ለእንስሳት መኖ የሚሆኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። ህብረተሰቡም የሚተከሉ ችግኞችን በመከታተልና አስፈላጊውን እንክብካቤ በማድረግ የደን ሽፋን ለመጨመር የበኩሉን እንዲወጣ ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አመርቂ ውጤት ተገኝቶበታል 
Apr 15, 2026 100
ወላይታ ሶዶ ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች አመርቂ ውጤት የተገኘባቸው መሆኑን የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ተናገሩ። በክልሉ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የበልግ ወቅት ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር "አረንጓዴ አሻራ ለተምሳሌት ሀገር ብልፅግና" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ሼላ ቦርኮሼ ቀበሌ ተካሂዷል።   የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጥ አመታት ተግባራዊ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አመርቂ ዉጤት ተገኝቶበታል፡፡ መርሃ ግብሩ የተራቆቱና ከጥቅም ውጭ የነበሩ መሬቶች ለምተው እንደገና ጥቅም እንዲሰጡ ከማድረጉ ባሻገር 18 ነጥብ 95 ከመቶ የነበረውን የክልሉን የደን ሽፋን ወደ 23 ነጥብ 86 ከመቶ በላይ ለማሳደግ ማስቻሉን ገልጸዋል። የችግኝ ተከላው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ በመሆኑም ለተያዘው የበልግ ወቅት የችግኝ ተከላም በቂ ዝግጅት መደረጉን አመልክተዋል። በዘርፉ የመጣውን ለውጥ ለማስቀጠልም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በነቂስ ወጥቶ ችግኝ መትከልና መንከባከብ እንደሚገባውም አሳስበዋል። በምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊና የዲላ ክላስተር አስባባሪ መሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸዉ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ ነዉ ብለዋል፡፡   በበጋው ወራትም 1 ሺህ 384 የማህበረሰብ ተፋሰስ ውስጥ 159 ሺህ ሄክታር መሬት በዋና ዋና የአፈርና ዉሃ ጥበቃ ስራዎች መሸፈናቸውም ገልጸዋል። በበልግ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የጥምር ደን ፣ የፍራፍሬ ፣ የሀገር በቀል እጽዋት፣ የቡና ፣ የእንሰት ፣የጥላና የጌጥ ዛፍ ችግኞች ተከላ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት በተካሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተጎድቶ የነበረውን የተፈጥሮ ሀብት መመለስ ተችሏል ያሉት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ናቸው፡፡   በአሁኑ ወቅትም በዞኑ 16 ተራራዎችን ለማልማት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዘንድሮ የበልግ ወቅት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ እንደሆንም አብራርተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 439
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 353
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 642
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት።   ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል።   የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው 
Mar 22, 2026 335
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሐተታዎች
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 13, 2026 200
በምግብ ራስን የመቻል ጉዞ አንዱ ምሰሶ - የስንዴ ልማት በሙሴ መለሰ ስንዴ በኢትዮጵያ በከፍትኛ ደረጀ ከሚመረቱና ለግብይት ከሚውሉ የሰብል ምርቶች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የስንዴ አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል በግንባር ቀደምነት ትጠቀሳለች። ከ2011/2012 የምርት ዘመን በፊት ኢትዮጵያ በመኸር የምታለማው ስንዴ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊየን ሔክታር ያልበለጠ ነበር። የበጋ መስኖ ስንዴ ሲጀመርም 3 ሺህ ሔክታር ብቻ እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በመኸር፣ በበጋ መስኖ እና በበልግ ወቅት 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ እያለማች እንደምትገኝ የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያስረዳል። ሚኒስቴሩ የ2018 ዓ.ም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፤ 4 ነጥብ 29 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ በማልማት ከበጋ መስኖ ስንዴ 175 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን መግለጹ ይታወሳል። በኢትዮጵያ በአብዛኛው የስንዴ ምርት የሚመረተው በአነስተኛ አርሶ አደሮች ነው። ባለፉት ዓመታት ግን የሜካናይዝድ እርሻ የስንዴ ምርቱን በእጥፍ እንደጨመረው ይገለጻል። መንግሥት መስኖን በመጠቀም ስንዴን በዓመት አንድ ጊዜ ከማምረት ወደ ሦስት ጊዜ ማምረት የሚቻልበትን አሰራር በመፍጠር የሀገሪቱን ምርታማነት ለማሳደግ እየሠራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ107 ሚሊየን ኩንታል በላይ ነው። ይህንን ፍላጎቷን ለመሙላት ለዓመታት ከ700 ሚሊየን ዶላር እስከ 1 ቢሊየን ዶላር ለስንዴ ግዥ ወጪ ታደርግ ነበር። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ትሸፍን የነበረውም ከውጭ በምትገዛው ስንዴ ነበር። መንግሥት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በማስፋፋትና በየዓመቱ የሚመረትበትን ዙር በመጨመር ኢትዮጵያ የስንዴ ፍጆታዋን ሙሉ በሙሉ እንድትሸፍን በትኩረት ሲሠራ ቆይቷል። በዚሁ በ2014 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገር ስንዴ ማስገባት አቆመች። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያገኘችው ውጤት ከውጭ ማስገባትን ማስቆም ብቻ አልነበረም። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ራስን ብቻ ሳይሆን ኤክስፖርት የማድረግ ዐቅም እንዳላት በመግለጽ፤ ስንዴ ወደ ውጪ መላክ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስቀመጡት ሀገራዊ ግብ መሰረት ኢትዮጵያ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ውጭ የመላክ ተግባርን በይፋ አስጀምራለች። የስንዴ ኤክስፖርቱ ኢትዮጵያ ገጽታዋን የሚለውጥ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ መግባቷን የሚያመላክት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ገልጸው ነበር። ኢትዮጵያ በ2015 ዓ.ም የሀገር ውስጥ ፍጆታዋን ሸፍና 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ለውጭ ገበያ የማቅረብ ዐቅም እንዳላት ብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚና የኤክስፖርት ኮሚቴ አረጋግጧል። ኮሚቴው የሀገራዊ የነፍስ ወከፍ ፍጆታና የሀገሪቱን አጠቃላይ የምርት ሚዛን በማጥናት ከፍጆታ የሚተርፍ 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ወደ ውጭ መላክ እንደሚቻልም ተገልጿል። 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ባሳለፍነው የካቲት ወር በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄዱ የሚታወስ ነው። በወቅቱም የአፍሪካ ሕብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ከጉባዔው ጎን ለጎን በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ ተምሳሌታዊ የሆነ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ የስንዴ ምርታማነቷን በማሳደግ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈን ባለፈ ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሏን ሕብረቱ መመልከት መቻሉንም ተናግረዋል። የአፍሪካ ሀገራት በዓመት ውስጥ ለምግብ ምርቶች ከሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ ስንዴ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዝም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከውጭ የሚገባውን ምርት በሀገር ውስጥ ስንዴ መተካት እንደሚቻል በተግባር ያሳየችበት መንገድ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የኢትዮጵያን ተሞክሮ ወስደው ወደ ተግባር እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ሥራ ላይ እያሳየች ያለውን ሥራ አስፍታ ከቀጠለች በምግብ ራሷን የመቻል ሕልሟን የማሳካት እድሏ ሰፊ መሆኑንም ማመላከታቸው ይታወሳል።
የጤና ነገር ...
Apr 3, 2026 2155
በዮሐንስ ደርበው የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። የኒውትሬሽን ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ የሰው ልጅ የሰውነት ክፍል 60 በመቶው ውኃ እንደመሆኑ ለተስተካከለ ጤና ሚዛን መጠበቅ በቂ ውኃ መጠጣት ይገባል። ውኃን በትክክለኛው መጠንና ጊዜ መውሰድ ከተቻለ የኩላሊት ህመም ተጋላጭነትን 50 በመቶ መቀነስ እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ነገር ግን ሰውነት የሚፈልገውን የውኃ መጠን በአግባቡ ካላገኘ ለዕለታዊ እና በጊዜ ሂደት ሥር ለሚሰድዱ ህመሞች የመጋለጥ ዕድል እንደሚጨምርም ያነሳሉ። ለመሆኑ ሰውነት የሚፈልገውና በቂ የውኃ መጠን የሚባለው መጠኑ ስንት ነው? በቂ ውኃ አለመጠጣትስ የሚያስከትለው ችግር ምንድን ነው? በሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎች ላይ የኒውትሬሽን መምህር፣ ተመራማሪ እና ደራሲ ይሁኔ አየለ ምላሽ አላቸው። አንድ ሰው የሚያስፈልገው የውኃ መጠን በዕድሜ፣ ጾታ፣ በሥራ ባሕርይ፣ በመኖርያ አካባቢ፣ እንደ ጤና ሁኔታው እና እንደ ሰውነት ክብደቱ እንደሚወሰንም በምላሻቸው አስገንዝበዋል። ለምሳሌ የስኳር ታማሚዎች፣ የምታጠባ እናት፣ በዕድሜ የገፉ ሰዎች፣ ብዙ አድካሚና ላብ የሚያወጡ፣ በሞቃታማ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች በቀን 3 ሊትር ውኃ መጠጣት አለባቸው ይላሉ። በአማካይ ግን በቀን አንድ ሰው ከ2 እስከ 3 ሊትር ውኃ መጠጣት እንደሚጠበቅበት ይገልጻሉ። ጤናማ ሕይወት የሚመሠረተው ከውኃ ነው፤ ለምሳሌ ውኃማውን 60 በመቶ የሰውነት ክፍል ሚዛን ለማስጠበቅ የግድ አስፈላጊውን መጠን ውኃ መጠጣት እንደሚገባ ይመክራሉ። በሰውነት ውስጥ የሚካሄደው ሕይወታዊ ሂደት (ባዮሎጂካል ፕሮሰስ) ውኃን መሠረት ያደረገ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለምሳሌ ለተስተካከለ የሥርዓተ-ምግብ ሂደት፣ ቆሻሻን ከሰውነት አጣርቶ ለማስወጣት፣ የአጥንት መገጣጠሚያ ሥራን ለማስተካከል እና ለሌሎችም በርካታ የሰውነት ክፍሎች የተሳለጠ ተግባር ውኃ ቁልፍ መሆኑን አንስተዋል። ይህን ተከትሎም ውኃ ካሎሪ አልባው መድኃኒት (ተፈጥሯዊው መድኃኒት) እስከመባል መድረሱን ነው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ያስረዱት። ሰውነት የሚያስፈልገውን ያህል ውኃ አለመጠጣት ግን ድካም ያስከትላል፤ ለማየት፣ ለመንቀሳቀስ፣ ለመሥራት፣ ለማሰብ፣ ለመረጋጋት . . . አያስችልምና ሲሉ ያብራራሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንድ ሰው ውኃ የመጠማት መጠኑ ከአራት በመቶ በላይ ከሆነ ለሞት ሊጋለጥ እንደሚችልም ጠቅሰዋል። ውኃ አለመጠጣት፤ የጨጓራ ህመምን በማባባስ ማስገሳት፣ የቆዳ ድርቀትና ግርጣት፣ የኩላሊት ህመም ሌሎች የሰውነት ክፍሎችም ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሠሩ ያደርጋል ነው ያሉት። ከምግብ በፊት 30 ደቂቃ ቀድሞ ውኃ መጠጣት ውፍረትን ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በቂ ውኃ ከመጠጣት በተጨማሪ ፍራፍሬዎችንና አትክልቶችን ማዘውተር እንደሚመከርም ገልጸዋል። የፈላ ውኃ እና የዝናብ ውኃን በብዛት መጠጣት በሰውነት ውስጥ ያሉ ንጥረ ነገሮችን በማስወገድና በኩላሊት ላይም ጫና እንደሚፈጥር አመላክተዋል። ለተስተካከለ ጤናማ ሕይወት የግድ ውኃ መጠጣትን ልማድ ማድረግ እንደሚገባም ይመክራሉ። #ውኃ_መጠጣት #ጤና #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency
ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች
Apr 3, 2026 2267
በዮሐንስ ደርበው የለውጡ መንግሥት ኢትዮጵያን ማሥተዳደር ከጀመረ እነሆ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ላይ 8 ዓመት ሞላው። በእነዚህ ዓመታት በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚው፣ በማኅበራዊ ዘርፉ በዲፕሎማሲውና በሌሎችም መስኮች የተለያዩ ስኬቶች ተከናውነዋል። በእነዚህ ጥቂት ዓመታትም ለማሳካት ቀርቶ ለማሳብ የማይደፈሩ ብዙ ውጤቶችም ተመዝግበዋል። የተገኙት ስኬቶች ከጊዜያቸው የፈጠኑ ናቸው። ለዚህም ሕዝቡ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በነቂስ እየወጣ አድናቆቱን ገልጿል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሰጡት የሰላ አመራርነትና ቁርጠኝነትም አክብሮቱንና ምሥጋናውን ገልጿል። የለውጡ መንግሥት አካሄድ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የልማት ፕሮጀክቶችም በይበልጥ ተስፋፍተውና ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መንግሥት ለሚያደርገው ጥረት ከጎኑ እንደሚቆሙም በድጋፍ ሰልፍ ላይ ባስተጋቧቸው መልዕክቶቻቸው አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ በለውጡ መንግሥት ለማሳካት ቀርቶ ለማሰብ የማይደፈሩ ተግባራት ተከናውነዋል። ከእነዚህ ከፍተኛ ጥቅም ከተገኘባቸው የታሪክ እጥፋትን ካሠረጹ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል ጥቂቶቹን ቀጥለን በወፍ በረር እንዳሥሣለን። ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ሥልጣኔ - በምርጫ ካርድ መምረጥ የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። • የኮሪደር ልማት እንደምናውቀው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነትና ልዩ ትኩረት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከሁሉም አስቀድሞ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ ነው። አሁን ላይ ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የበርካታ ከተሞችን ገጽታ የቀየሩ አስደማሚ ሥራዎች ተከናውነውበታል። ይህም በገጠር ጭምር ተጠናክሮ የቀጠለ ጉዳይ ነው። ለዘመናት አሮጌ ገጽታዋን ይዛ ያሸለበችውን አዲስ አበባ እንደ አዲስ የፈጠራትም ይኸው ፕሮጀክት ነው። አሁን ላይ መዲናይቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን ለውጥ ዐይተው ዝም ማለት አልቻሉም። ከመደመማቸው አንጻር የዘወትር አጀንዳቸውም እያደረጓት ይገኛሉ። ይህንን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት፤ ኮሪደር ልማት ማለት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት ነው ማለታቸው ይታወሳል። ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑንንም አስረድተዋል። ከለውጡ መንግሥት ዐበይት የትኩረት መስኮች አንዱ የሆነውን የቱሪዝም ዘርፉን እንቅስቃሴ ለማሳደግም ቁልፍ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ ድርብርብ ፕሮጀክት ነው የኮሪደር ልማት። • የበጋ መስኖ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የለውጡ መንግሥት ዋነኛ ትኩረቱ ነው። ለዚህም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አንዱ ማሳኪያ ሥልት አድርጎ እየተጋ ይገኛል። የበጋ መስኖ ስንዴ ኢትዮጵያ ስንዴን ከውጭ ማስገባት አቁማ መላክ እንድትጀምር ያስቻለ ኢኒሼቲቭ ነው። በዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችና በሜካናይዜሽን ታግዞ በስፋት እየተሠራበትም ይገኛል። ከለውጡ መንግሥት ወዲህ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ምክንያት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በምርታማነት ማደግና የሥራ ዕድል በመፍጠር አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብም ከፍተኛ ውጤት ተገኝቶበታል። ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ ስንዴ ላይ ባሳየችው ትጋት፤ ፍጆታዋን በራሷ ዐቅም የሸፈነችው፣ ስንዴን ከውጭ ማስገባትን ያቆመችው፤ ስንዴን ወደ ውጭ መላክ የጀመረችው በለውጡ መንግሥት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ በመሸለም ለጥረታቸው ዕውቅና መስጠቱም ይታወሳል። • መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀደም ሲል አንድ ጉዳይን ለማስፈጸም እዚያም እዚህም መንከራተት የግድ ነበር። በዚህ አያበቃምና ወረፋውም ሌላ ችግር ነው። መንግሥት በተለያዩ መድረኮች ባካሄዳቸው ሕዝባዊ ውይይቶች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉልን የሚሉ እሮሮዎች በረከቱ። መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል ሥራ ወደ ተግባር አሥገባ። በዚህም መሠረት ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ ጀመረ። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነውም አሉ። ለዚህ ቁርጠኝነታችን አንዱ ማሳያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመራቸውንም ገለጹ። እንግዲህ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ አንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ ታግዘው በተሳለጠ ሂደት እንዲሰጡ በማድረግ የተገልጋይን እንግልት፣ ገንዘብ እና ጊዜ መቀነስ ያስቻለ አሠራር ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት ተደርጎም ይወሰዳል። በየከተሞቹም እየተስፋፋ ነው። • አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ አይ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ተጠቃሚ እንድትሆን ከፍተኛ ጉጉት እንዳላቸው በቁጭት በተለያዩ መድረኮች ያነሳሉ። ለዚህም መፍትሔ ዘይደው ተቋማትን ከማቋቋም ጀምሮ ለዘርፉ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ ተግተዋል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂው ጋር አብሮ ለመጓዝ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን አቋቋመች። የኤ አይ ዩኒቨርሲቲ በመክፈት በግብርናው፣ በጤናው እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠርም በሂደት ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት ቀይሮ ወደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ሕንፃ በተዛወረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአምስት ዓመት ውስጥ አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ መድረሱ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ የሮቦቶችን ሶፍትዌር ብቻ ሳይሆን ውጫዊ የአካል ክፍልን (ሃርድዌር) መሥራት ጀምሯል ብለዋል። ድሮን ማምረት ብቻ ሳይሆን የማነጋገር ዐቅም እየፈጠረ ያለ ተቋም መሆኑንም አንስተዋል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ደረጃ የሚወዳደር አሠራርን የሚከተል መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ምርቶችን አውጥቷል ማለታቸው ይታወቃል። ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮሉሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን ሲሉ ማስገንዘባቸውም ይታወሳል። • የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው። በዚህ ሂደት ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊታአውራሪነት ይጠቀሳል። በተደራጀና ተቋማዊ ሆኖ ባልተቆራረጠ አካሄድ እየተከናወነ ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተተከሉ ችግኞችም በየዘርፉ ተጠቃሚነት አድጓል፤ ተጠናክሮም ይቀጥላል። • የሌማት ትሩፋት ከመጋቢት ሥጦታዎች አንዱ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ነው። የምርት አቅርቦትን በማስፋት ለተረጋጋ ግብይት እና ለተመጣጠነ ሥርዓተ-ምግብ ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከት ላይም ይገኛል። ኢኒሼቲቩ ለግብርና ኢንቨስትመንትና ለሀገራዊ የሥርዓተ-ምግብ መሻሻል ጉልኅ ሚና እየተጫወተ ነው። የዋጋ ንረትን በማረጋጋት፣ የምርት ስብጥርን በማሳደግና በዘላቂነት በማቅረብ ረገድም የጎላ ሚና አለው። የግድ ሰፋፊ መሬት መፈለግ ሳያሻ በትንሽ ቦታ ብዙ በማምረት ፍጆታን ከመሸፈን አልፎ ኢኮኖሚን በመደጎም እና የሥራ ዕድል በመፍጠርም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው። • የቱሪስት መዳረሻ ልማት ቅርሶች እንዲጠገኑ፣ አዳዲስ ሎጂዎች እንዲገነቡ፣ በመዳረሻ ስፍራዎች መሠረተ-ልማት እንዲሟላ ያስቻሉ ተግባራት በለውጡ መንግሥት ተከናውነዋል፤ አሁንም ተጠናክሮ የቀጠለ እና ስኬታማ ኢኒሼቲቭ ነው። በዚህ ሂደት ከሐሳብ አመንጭነት ባሻገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የጻፉትን መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ ጭምር ለቅርስ ጥገናና ለቤተ-መጻሕፍት ግንባታ እንዲውል አድርገዋል። በተጨማሪም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት፤ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ ወደ ተግባር አስገብተዋል። በእነዚህ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። አማራጭ የቱሪስት መዳረሻም ሆነዋል። • የተቋማት ግንባታ ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል መሪል ሐሳብ በተካሄደው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ፤ የተቋማት ግንባታና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ብለዋል። በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ሲሉም አስገንዝበዋል በወቅቱ። ዘመን የማይለውጣቸው ዘላቂ ጠንካራ ሃገራዊ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ብዙ ርቀት መጓዝም ተችሏል። በመሆኑም የመንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲሆኑ በማድረግ እና ሥርዓት በተለዋወጠ ቁጥር የማይፈርሱ ወይም የሚሻገሩ ተቋማት መገንባት ተችሏል። ይህ ትጋት ተጠናክሮም ቀጥሏል።
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3775
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … በኢዜአ ዐይን …! የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ትንታኔዎች
በፈተናዎች ሁሉ የጸናው የኢትዮጵያና የላይቤሪያ ወዳጅነት
Apr 14, 2026 1154
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያና ላይቤሪያ ዘመናትን የተሻገረ ወዳጅነት አላቸው። ይሄ ወዳጅነት በፈተናዎች ጊዜ ሁሉ ጸንቶ የዘለቀም ነው። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ ውስጥ ብቸኛ ነፃ ሀገራት በመሆናቸው፣ በዓለም አቀፍ መድረኮች (ለምሳሌ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ) የአፍሪካውያን ድምፅ ሆነው በጋራ ይቆሙም ነበር። የሀገራቱ የወዳጅነት እና የትብብር ስምምነትም እ.አ.አ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ የጀመረ ሲሆን፣ በመካከላቸው ያለው ዘላቂ ወዳጅነት እና በዓለም አቀፍ መድረኮች (እንደ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት) በጋራ ለመቆም ቃል የተገባበት ሰነድም ተደርጎ ይወሰዳል። የዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መሠረት የጣሉትም ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ እና ፕሬዝዳንት ዊሊያም ቱብማን ናቸው። እ.ኤ.አ. በ1954 ፕሬዝዳንት ቱብማን ወደ አዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ይፋዊ ግንኙነት እንዲጀመር በር ከፍቷል። ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ እ.አ.አ. 1958 ጉብኝት ወደ ሞንሮቪያ በማድረግ፣ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኙ የነፃነት ንቅናቄዎችን በጋራ ለመደገፍ ተወያይተዋል። እነዚህ ጉብኝቶች የሁለትዮሽ ብቻ ሳይሆኑ አህጉራዊ ፋይዳም ነበራቸው። እ.አ.አ በ1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ሲመሰረት፣ ሁለቱ ሀገራት "የሞንሮቪያ" እና "የካዛብላንካ" ቡድኖችን ልዩነት በውይይት በመፍታት ለአህጉሪቱ አንድነት የጀርባ አጥንት መሆናቸውን አስመስክረዋል። በ1960ዎቹ መጀመሪያ ላይ በ”ሞንሮቪያ ቡድን” እና "የካዛብላንካ ቡድን" መካከል የነበረውን ልዩነት ለማጥበብ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በጋራ በመስራታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሊመሰረት ችሏል። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በችግር ውስጥ የተፈተነ ወዳጅነት ነው የሚል ሀሳብ በብዙዎች ይነሳል። የዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ በላይቤሪያ የነበራት የሰላም ማስከበር ሚና ነው። ላይቤሪያ ለ14 ዓመታት በዘለቀው አውዳሚ የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት መንግሥታዊ መዋቅሯ ፈርሶ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2003 የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ሰላም እንዲያስከብሩ ከጠራቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ ነበረች። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ በርካታ ሰራዊቷን በማሰማራት ለሀገሪቷ ሰላም ዋጋ ከፍላለች። ሰራዊቱ አማፂያንን ትጥቅ በማስፈታት፣ ተዋጊዎች ከማህበረሰብ ጋር እንዲቀላቀሉ በማድረግ እና የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ከፍተኛ ስራ ሰርቷል። ዋና ከተማዋ ሞንሮቪያ እና በገጠራማ አካባቢዎች የተኩስ አቁም ስምምነቱ እንዳይጣስ ጥብቅ ቁጥጥር አድርጓል። የኢትዮጵያ ሰራዊት የጤና ቡድን በየሰፈሩ በመዘዋወር ለላይቤሪያውያን ነፃ የህክምና እርዳታ እና መድሃኒትም ይሰጥ ነበር። ሰራዊቱ የራሱን ስንቅ ለተቸሩ ዜጎች በማካፈል ወንድማማችነትን በተግባር አሳይቷል። እ.ኤ.አ በ2014 የኢቦላ ወረርሽኝ በላይቤሪያ በከፋ ሁኔታ በተከሰተበት ወቅትም፣ ሌሎች ሀገራት ሰራዊታቸውን ሲያስወጡ ኢትዮጵያ ግን የህክምና ቡድኖችን እና ሰራዊቷን በማቆየት ከላይቤሪያ ህዝብ ጎን ቆማች። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ ሶስት ተከታታይ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫዎች እንዲካሄዱ በሰላም ማስከበሩ ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የላይቤሪያ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች የላቀ አገልግሎት ሜዳሊያ እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ የነበራት የሰላም ማስከበር ሚና ከወታደራዊ ተልዕኮ ባለፈ የደም እና የአጥንት መስዋዕትነት ከፍላለች። ይህ የሰራዊቱ ተሳትፎ ዛሬም ድረስ በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ላለው ጥብቅ ወዳጅነት ዋነኛው ምክንያት ተደርጎ ይወሳል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራቱ መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች ለሁለትዮሽ ትብብሩ መጠናከር አስተዋጽኦ አድርገዋል። የቀድሞዋ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ እ.አ.አ በ2006 ስልጣን በያዙ ማግስት አዲስ አበባን ጎብኝተዋል። ይህም ኢትዮጵያ በላይቤሪያ ሰላም ለማስፈን ላደረገችው ድጋፍ እውቅና የሰጡበት ነበር። ሰርሊፍ በላይቤሪያ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ሲያበቃ እ.አ.አ ጁላይ 2015 ኢትዮጵያን በመጎብኘት ለተደረገላቸው የህክምና ቡድን ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። የቀድሞዋ ፕሬዝዳንት እ.አ.አ በ2017 ለሶስት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳላኝ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ፕሬዝዳንቷ በወቅቱ የሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክን የጎበኙ ሲሆን ላይቤሪያ ከኢትዮጵያ የጨርቃ ጨርቅ ልማት ዘርፍ ልምድ መቅሰም እንደምትፈልግ በወቅቱ ገልጸው ነበር። የላይቤሪያ የእግር ኳስ ኮከብ እና የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዊሃ እ.አ.አ በ2018 ስልጣን ከያዙ በኋላ በአዲስ አበባ በተካሄደው 30ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የተሳተፉ ሲሆን ከጉባኤው ጎን ለጎን ከወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ተገናኝተው በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ላይ ተወያይተዋል። የቀድሞው የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲ-ማክስዌል ሳህ ከማያህ እ.አ.አ በ2022 በአዲስ አበባ ጉብኝት በማድረግ በሁለቱ ሀገራት መካከል የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን (Joint Ministerial Commission) እንዲቋቋም ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በላይቤሪያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (UNMIL) ላይ በነበረበት ወቅት፣ የተለያዩ የመከላከያ ሚኒስትሮች እና የጦር አዛዦች የኢትዮጵያን ሰላም አስከባሪ ኃይል ለመጎብኘት እና ከላይቤሪያ ባለስልጣናት ጋር ለመወያየት በተደጋጋሚ ወደ ሞንሮቪያ ተጉዘዋል። ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ውይይቶች በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነቶችም ተፈራርመዋል። ሰላም ፣ ደህንነት፣ ጤና፣ የአየር አገልግሎት፣ የቪዛ ነፃ መብት ፣ የንግድ ትብብር ማዕቀፍ፣ ግብርና፣ ትምህርት፣ ባህል እና ስፖርት ስምምነት ከተደረገባቸው ዘርፎች መካከል ይጠቀሳሉ። የአየር አገልግሎት ስምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞንሮቪያ ያለምንም ገደብ እንዲበር እና ላይቤሪያን ከቀሪው ዓለም ጋር ማገናኘት የሚያስችል ህጋዊ ማዕቀፍ ነው። የሰላም ማስከበር ስምምነቱ በተባበሩት መንግሥታት ማዕቀፍ ውስጥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል እንድትልክ የተደረገው ስምምነት በላይቤሪያ መረጋጋት እንዲመጣ ትልቅ ድርሻ ነበረው። በኪነ-ጥበብ እና በስፖርት ዘርፍ (በተለይም በእግር ኳስ) የሁለቱ ሀገራት ወጣቶች ልምድ እንዲለዋወጡ የሚያስችሉ የመግባቢያ ሰነዶች ተፈርመዋል። የወቅቱ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦአከይ እ.አ.አ 2023 ፕሬዝዳንት ሆነው በተመረጡበት ወቅት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ለማደስ እና በንግድ ዘርፍ በጋራ ለመስራት ፍላጎታቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም ከተካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ከላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦአካይ ጋር ውይይት አድርገዋል። የሁለትዮሽ ውይይቱ በቴክኖሎጂ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ኢትዮጵያ ለመገንባት ባቀደችው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ላይ ያተኮረ ነበር። በውይይቶቹ ላይ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በንግድ እና ኢንቨስትመንት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። የላይቤሪያው ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ለስራ ጉብኝት ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክትም የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ የነገ ብሩህ ተስፋ እየተሰራባት ወደ ምትገኘው ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ እንኳን በሰላም መጡ ብለዋል። በፕሬዝዳንቱ ቆይታ እጅግ ፍሬያማ ውይይት እንደሚኖራቸውም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። የፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ የስራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ወዳጅነት የበለጠ እንደሚያጠናክርም ታምኖበታል። የኢትዮጵያ እና የላይቤሪያ መጻኢ ግንኙነት ከታሪካዊ ወዳጅነት ወደ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ አጋርነት የማሳደግ ፍላጎት በሁለቱም ወገን በኩል አለ። በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የአቪዬሽን ትስስር፣ የቴክኖሎጂ ልውውጥ እና በአህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጠና (AfCFTA) ማዕቀፍ የሚደረግ ትብብር ለጋራ ብልጽግና መሰረት ይጥላል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 11, 2026 175
ከመጋቢት 27 እስከ ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦ • ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ የትንሣኤ በዓል በክርስቲያኖች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው በዓል ነው፤ ሞት የተሻረበትና ሕይወት ዋስትና ያገኘበት ነው ብለዋል። የትንሣኤ በዓል ከሞት ባሻገር ሕይወት ከመቃብር ባሻገር ትንሣኤ መኖሩ የታወጀበት መሆኑንም ገልፀው፤ ሞት መጨረሻ መቃብር መዳረሻ አለመሆናቸው የተረጋገጠበት ነው ብለዋል በመልዕክታቸው። የዘንድሮውን ትንሣኤ የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በሚያልፍ ፈተና ውስጥ እንዳለች እያሰብን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን ሲሉ ገልፀዋል። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ በጥልቁ ጨለማ ጠፍተን እንድንቀር አሥረው ለመያዝ የሚሞክሩ ወጥመዶች ብዙ ናቸው፤ ወደ ተስፋ ምድር እንዳንሻገር የሚጎትቱ ሰበቦች ሞልተዋል፤ ዳሩ ግን ከሕማማቱ ወዲያ ትንሣኤ ከዕንቅፋቱ ባሻገር ስኬት እንደሚጠብቀን አምነን እንታገላለን ሲሉም አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ትንሣኤ መቃረቧን ገልፀው፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ከሚበሰርባቸው ምዕራፎች አንዱ ግንቦት ላይ የሚካሄደው ምርጫ መሆኑንም አመላክተዋል። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም ብለዋል። • የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሁለት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ካደረጉት የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት ኢቫሪስቴ ንድያይሺሚዬ ጋር ውጤታማ የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን ባሳለፍነው ሳምንት ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ለማጠናከር ያለሙ በርካታ የመግባቢያ ሰነዶች ፊርማ አከናውነናል ሲሉም አስታውቀዋል። ስምምነቶቹ ለሁለቱም ሀገራት የበለጸገ እና የተባበረ መጻኢ ዕድልን የሚያረጋግጡ የቆዩ ግንኙነቶቻችንን ወደ ተጨባጭ ትብብር ለመቀየር እንደ ወሳኝ መሠረት የሚያገለግሉ የጋራ ቁርጠኝነታችን ማሳያ ጭምር ናቸው ብለዋል። ጉብኝታቸውን እንዳጠናቀቁም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው ሸኝተዋቸዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪኤግዚም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኢሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም ስትራቴጂካዊ ግንኙነታችንን በምናጠናክርባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረናል ብለዋል። • የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሥተዳደር ዓመታዊ አፈጻጸም ግምገማ ባሳላፍነው ማክሰኞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሥተዳደር ፕሬዚዳንት ሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦላቸው በውጤቶቹ ላይ ግምገማ እና ውይይት አድርገዋል። • የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ሹመት መራዘም በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 62(9) እና በዐዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀፅ 2(ለ) መሠረት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አሥተዳደርን በርዕሰ መሥተዳደርነት እንዲመሩ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አሥተዳደር አስመልክቶ በጸደቀው ደንብ ቁጥር 479/2013 አንቀጽ 4(2) እና የዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ባቀረቡት መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደን ሹመት ለአንድ ዓመት አራዝመዋል። • ማዕድ ማጋራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች እና ጽሕፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሕጻናት ማዕድ አጋርተዋል። • የአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ኅልፈተ ሕይወት አምባሳደር ቆንጅት፤ በዲፕሎማሲው መስክ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ላበረከቱት ጉልኅ አስተዋጽዖ፣ ለሰጡት አስተምኅሮና ለነበራቸው ብልኅ አመራር ምንጊዜም ሲታወሱ እንደሚኖሩ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባስተላለፉት የኀዘን መግለጫ መልዕክት ገልጸዋል። ትጉኅና ከብረት የጠነከሩ ዲፕሎማት ነበሩ በማለት ለሙያቸው የነበራቸውን ጽኑ አቋምና የሀገር ፍቅር ስሜትም አንስተዋል። ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት በማረፋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሰማቸውን ኀዘን ገልጸዋል። አምባሳደሯ ለሕግ፣ ለአሠራር፣ ለፕሮቶኮል እና ለኢትዮጵያ ጥቅሞች በነበራቸው የጸና አቋም እናስታውሳቸዋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከእርሳቸው በኋላ አያሌ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል ብለዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባስተላለፉት የኀዘን መግለጫ መልዕክት፤ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ እና ታላቅ ዐሻራን ማሳረፍ የቻሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ጥልቅ ኀዘን ተሰምቶኛል ብለዋል። አምባሳደር ቆንጂት እስከ ከፍተኛ ዲፕሎማትነት በደረሰ ረጅም የሥራ ዘመናቸው ለሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ያስመዘገቡት ድል እና ያበረከቱት አስተዋጽዖ ሁልጊዜም በክብር የሚታወስ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ባሳለፍነው ሳምንት “ፖሊሳዊ አንድነት ለዘላቂ ሰላም” በሚል መሪ ሐሳብ 20ኛው የፖሊስ ኮሚሽነሮች መክፈቻ ጉባዔ ተካሂዷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፤ የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያ ፖሊስ በሚሰጠው አገልግሎት ታማኝም አሳማኝም መሆን አለበት ብሎ ያምናል ብለዋል። የፖሊስ ኃይላችን የጥፋት ኃይሎች በሀገራችንና በሕዝባችን ላይ የሰነዘሩትን ጥቃት በአንድነት በመቆምና መስዋዕትነት በመክፈል ቀልብሷል፤ ይህም ለሁላችንም ኩራት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የፖሊስ አመራሮችና የሠራዊቱ አባላት በዕውቀት፣ በታማኝነትና በሕዝብ አገልጋይነት ሥነ-ልቦና ለላቀ ተልዕኮ እንድትዘጋጁ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
ከፓን አፍሪካኒዝም እስከ ኢኮኖሚያዊ አጋርነት - የኢትዮጵያ እና ብሩንዲ የስድስት አስርት ዓመታት የዲፕሎማሲ ጉዞ
Apr 9, 2026 485
በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያና የብሩንዲ ግንኙነት የሚጀምረው አፍሪካ ከቅኝ አገዛዝ ቀንበር ለመውጣት በምትታገልበት ወሳኝ ወቅት እንደነበረ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። ኢትዮጵያ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌት እንደመሆኗ፣ ብሩንዲ እ.ኤ.አ በ1962 ከቤልጂየም ቅኝ አገዛዝ ወጥታ ነፃነቷን ስታገኝ ግንኙነታቸውን በይፋ ከጀመሩ የመጀመሪያዎቹ አገራት ተርታ ትመደባለች። ይህ ግንኙነት በወቅቱ በነበረው የፓን-አፍሪካዊነት መንፈስ እና አፍሪካዊ መፍትሄ ለአፍሪካዊ ችግሮች በሚለው መርህ ላይ የቆመ ነበር። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ምስረታ ላይ የነበራቸው የጋራ ተሳትፎ ለዘመናት ለዘለቀው ወንድማማችነት ጠንካራ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጧል። ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ አዳዲስ ከቅኝ ግዛት ነፃ የሚወጡ የአፍሪካ ሀገራትን ወደ አህጉራዊው መድረክ ለማምጣት በነበራቸው ራዕይ መሰረት፣ ከብሩንዲ የመጀመሪያው ንጉሥ ምዋሚ ምዋቡትሳ አራተኛ ጋር የጠበቀ ግንኙነት መስርተዋል። ግንኙነቱ በይፋ ከተጀመረ ከአንድ ዓመት በኋላም (እ.አ.አ 1963) ብሩንዲ በአዲስ አበባ በተመሰረተው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) ላይ በመስራች አባልነት እንድትሳተፍ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ድጋፍ አድርጋለች። በወቅቱ የነበረው የሀገራቱ ግንኙነት በፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል እና በቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ የተመሰረተ ነበር። በወቅቱ ይደረጉ በነበሩ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ስብስባዎች ላይ ኢትዮጵያ እና ብሩንዲ አህጉራዊ አጀንዳዎችን በጋራ አንጸባርቀዋል። ኢትዮጵያ በብሩንዲ የሰላም ሂደት ውስጥ ትልቅ ሚና ተጫውታለች። በተለይም በብሩንዲ የነበረውን የእርስ በርስ ጦርነት ለማስቆም በተደረገው ጥረት እና በአፍሪካ ህብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (AMIB) ውስጥ የኢትዮጵያ ሰራዊት ቀዳሚ ተሳትፎ ነበረው። ልዑኩ በአፍሪካ ህብረት ታሪክ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ በአህጉሪቱ የተመራና የተደራጀ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንደሆነ ይወሳል። ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ እና ከሞዛምቢክ ጋር በመሆን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት ልካለች። ሰራዊቱ የተኩስ አቁም ስምምነቱ እንዲከበር ማድረግ፣ ታጣቂዎችን ትጥቅ ማስፈታት እና ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረግ (DDR) ላይ ትልቅ ስራ ሰርቷል። ኢትዮጵያ በወታደራዊ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በዲፕሎማሲው ረገድም ንቁ ተሳትፎ አድርጋለች። የአሩሻ የሰላም ስምምነት እንዲሳካ እና በብሩንዲ የሽግግር መንግስት እንዲመሰረት በወቅቱ የነበሩ የኢትዮጵያ መሪዎች በኢጋድ (IGAD) እና በአፍሪካ ህብረት በኩል ጫና ሲያደርጉና ሲያሸማግሉ ቆይተዋል። በብሩንዲ በተለያዩ ቡድኖች መካከል እምነት እንዲገነባ ኢትዮጵያ እንደ ገለልተኛ እና ታማኝ አደራዳሪ ትታይ ነበር። ተልዕኮው ስራውን አጠናቆ ወደ ተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (ONUB) ሲቀየርም የኢትዮጵያ ሰራዊት እዛው በመቆየት ለሰላሙ ዘላቂነት አስተዋፅኦ ማድረጉን ቀጥሏል። ይህም ኢትዮጵያ ለቀጣናዊ ሰላም ያላትን ቁርጠኝነት አሳይቷል። ይህም በሁለቱ ሀገራት ትብብር ውስጥ በትልቁ የሚነሳ እና የሚወሳ ነው። በፓን አፍሪካኒዝም እና በፖለቲካዊ ወዳጅነት ላይ መሰረት አድርጎ የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ተለያዩ መስኮች እየሰፋ መጥቷል። እ.አ.አ በ1970ዎቹ መጀመሪያ በሀገራቱ መካከል የተፈረሙ የንግድ እና የባህልን ትብብር የማጠናከር የጋራ መግባቢያ ሰነዶች የዚሁ ማሳያ ናቸው። ባለፉት ዓመታት በሀገራቱ መካከል የተደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እና የጋራ ስብሰባዎች ግንኙነቱን ከማጠናከር ባለፈ የትብብር አድማሱን ማስፋትን ከግምት ውስጥ ያስገቡ መሆናቸውን ማየት ይቻላል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እ.አ.አ በ2023 በብሩንዲ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ በኢትዮጵያ እና ብሩንዲ መካከል ያለውን የኢኮኖሚ፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ አቪዬሽን እና ቀጣናዊ ሰላም ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ነው። በጉብኝቱ ወቅት ብሩንዲ የኢትዮጵያን የስንዴ ልማት እና የአረንጓዴ አሻራ ተሞክሮ በስፋት ለመተግበር ያላትን ፍላጎት አሳይታለች። የሁለትዮሽ ውይይቱ የተለያዩ ውጤቶች የተገኙበት ነው። በሁለቱ ሀገራት መካከል የንግድ ልውውጥን የሚያቀላጥፉ ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ ውሳኔ ተላልፏል። ኢትዮጵያ ለብሩንዲ በቴክኒክ እና በሙያ ስልጠና (TVET) ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብታለች። የሀገራቱ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን (JMC) በየጊዜው እየተገናኘ ስምምነቶችን እንዲከታተል መመሪያ ተሰጥቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከውይይቱ በተጨማሪ ግብርና እና ኢንዱስትሪን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2023ቱ የብሩንዲ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በማጠናከር ረገድ በዋና ማሳያነት የሚጠቀስ ነው። የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ እ.አ.አ በ2021 በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በጉብኝቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለብሩንዲ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ችግኞችን በስጦታ አበርክተው ነበር። ይህም ሀገራቱ በግብርና እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ያላችውን ፍላጎት የሚያሳይ ነበር። በፕሬዝዳንቱ ጉብኝት ወቅት የመጀመሪያ የኢትዮ-ብሩንዲ የመጀመሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባ ተደርጓል። በወቅቱ በግብርና፣ በቱሪዝም እና በትምህርት ዘርፍ አዳዲስ የመግባቢያ ሰነዶች ተፈርመዋል። እ.አ.አ በ2023 የብሩንዲ ፓርላማ የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን (CFA) በህግ አፀደቀ (Ratified)፤ ይህም ለኢትዮጵያ ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል ተደርጎ ተቆጠረ። ኢትዮጵያ ብሩንዲ ስምምነቱን እንድታጸድቅ ድጋፍ አድርጋለች። ይህም የሀገራቱን የውሃ ትብብር የበለጠ ያጸና ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የቀድሞው የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ፒዬር ንኩሩንዚዛ እ.አ.አ በ2012 በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል። ይህም በሀገራቱ የከፍተኛ አመራሮች የጉብኝት ልውውጦች ውስጥ የሚጠቀስ ነው። ከንኩሩንዚዛ ጉብኝት ሁለት ዓመታት በኋላ እ.አ.አ በ2014 ብሩንዲ በኢትዮጵያ ኤምባሲዋን ከፍታለች። ይህም የሀገራቱን ትብብር ለማጠናከር የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው። ኢትዮጵያ ከብሩንዲ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ስራ የሚሸፍነው በካምፓላ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ነው። ኢትዮጵያ እና ብሩንዲ በተለያዩ ጊዜያት ተደራራቢ ታክስን ማስቀረት፣ በኢንቨስትመንት፣ አየር ትራንስፖርት፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በመከላከያ እና ፀጥታ፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲሁም ባህልና ስፖርት ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶች ተፈራርመዋል። ጉብኝቶችና ስምምነቶች ኢትዮጵያና ብሩንዲ ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ትብብር በማሳለጥ እና የጋራ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድ ያላቸው ሚና ወሳኝ ነው። ሁለተኛው የኢትዮጵያና የብሩንዲ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን (Joint Ministerial Commission - JMC) መጋቢት 29 እና 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሄዷል። ስብስባውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ፣ የቀጣናዊ ትስስርና የልማት ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና በጋራ መርተውታል። በተጨማሪም የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና የዘርፍ ባለሙያዎች ተገኝተዋል። በስብስባው ማብቂያ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶች ተፈርመዋል። ስምምነቶቹም በዋናነት በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር (በተለይም በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ)፣ በግብርና ምርታማነት፣ በአቪዬሽን እና በቀጣናዊ ደህንነት ዙሪያ ላይ ያተኮሩ ናቸው። ስብስባው የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠናን (AfCFTA) መርህ መሰረት በማድረግ የሁለቱን ሀገራት የኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር፣ የመሰረተ ልማት ግንኙነቶችን ማስፋፋት እና በአባይ ተፋሰስ የጋራ ተጠቃሚነት ዙሪያ ተቀራርቦ ለመስራት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ሰነድ በመፈረም በስኬት ተጠናቋል። ውይይቱ የኢትዮጵያ እና የብሩንዲን ትብብር የበለጠ ማጠናከር የሚያስችል ነው። የቡሩንዲ ፕሬዝዳንትና የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸው የሁለቱን ሀገራት ትብብር ከማጠናከር ባለፈ በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትስስር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። የኢትዮጵያ እና የብሩንዲ መጻኢ የሁለትዮሽ ትብብር በሁለገብ ዘርፎች ላይ ያተኮረና ወደ ላቀ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚሸጋገርበት ወቅት እንደሚሆን ይጠበቃል። የፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ጉብኝት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽኑ ውሳኔዎች፣ ለቀጣዮቹ ዓመታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ለሚኖረው ጠንካራ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ትስስር መጠናከር ጉልህ ሚና ይኖረዋል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 4, 2026 1170
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 20 እስከ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ስለ አዲስ አበባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ አዲስ አበባ ከዋና ከተማ በላይ መሆኗን ገልጸው፤ በፈጣን እንቅስቃሴ ላይ ያለች፣ ወደ ኢትዮጵያ ነገ የመግቢያ በር፣ በፍጥነት እየተለወጠች ያለች የሀገር የልብ ትርታ፣ ሁሉንም አሳታፊ እና አርቆ አሳቢ የሆነ የከተማ ልማት ትልማችን መገለጫ ናት ብለዋል። ፈጣን መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት፣ የዘመናዊ ከተማ መፍትሔዎችን በማቅረብ፣ አካታች በሆነ መልኩ መኖሪያ ቤት በመገንባት እና ዘላቂ ዕድገትን በማረጋገጥ እየሠራን ያለነው ዛሬን ብቻ ሳይሆን ለነገው ትውልድ ጭምር ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ የሚገኙ ከተሞቻችን ሰዎችን ለማብቃት፣ ዐቅምን ለመጠቀም እና ዘላቂ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ ቅርጽ ይዘዋልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። • አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መርቀው ከፍተዋል። ‎በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው ብለዋል በወቅቱ። ‎የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን እንዲሁም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከል ማከተቱን አብራርተዋል። ‎ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። • የአዲስ ስፖርት ፓርክ መመረቅ ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)‎ የከተማችንን እድሳት ለማፋጠን እና የዜጎቻችንን ክብር ለመመለስ የገባነውን ቃል አንዱ ማረጋገጫ የሆነውን የአዲስ ስፖርት ፓርክን በይፋ መርቀን ከፍተናል ብለዋል። ‎በ5 ነጥብ 7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ፕሮጀክት፤ በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ 15 አትሌቶችን የሚዘክሩ የክብር ሐውልቶችን በፓርኩ መሃል በማቆም፣ የጀግኖቻችን ታሪክ ለተተኪ ትውልድ ስፖርተኞች ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋልም ነው ያሉት። የኦሎምፒክ ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ኳስ፣ የቅርጫት ኳስና የሜዳ ቴኒስ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የ800 ሜትር የሩጫ ትራክን ጨምሮ፤ እያንዳንዱ የዚህ ማዕከል ክፍል የዓለም አቀፍ መስፈርቶችን እንዲያሟላ ተደርጎ ተገንብቷል ሲሉም ገልፀዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በአፋር ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፋር ክልል ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት በአዋሽ ወንዝ ተፋሰስ በመሥኖ እየለማ ያለው የሱፍ ምርት ለተሻገረ ግብርና እና ለተሻገረ ገጠር ራዕያችን ተደማሪ ሃብት ነው ብለዋል። በአፋር ክልል ያየነው በመሥኖ ተፋሰስ በረሃ የመሰለውን ምድር የምርት መትረፍረፊያ የማድረግ ትጋት፤ ለሌሎች በተለይም ከዓመት እስከ ዓመት ዝናብ አጠር አካባቢዎች ትልቅ የመማሪያ ሠነድ እንደሚሆን አመላክተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በተካሄደው "የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ቅንጅት ለሀገራዊ ሰላም እና ደኅንነት" በሚል መሪ ሐሳብ በተካሄደው ብሔራዊ የደኅንነት ኮንፈረንስ ላይ የተሳተፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የጸጥታና ደኅንነት ተቋሞቻችን ችግርን ወደ ዕድል እንዲቀየሩ ያስቻሉ ናቸው ብለዋል፡፡ ጉዟችን ተጀመረ እንጂ አልተቋጨምና ከትናንት ዕዳዎች ተላቀን፣ የዛሬ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን ለነገው ትውልድ የምትመጥን ሀገር ለመገንባት በዓላማ ጽናት እንቀጥላለን ሲሉም አመላክተዋል። • ስለ መጋቢት 24 መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ወደ ሥልጣን የመጣውን የለውጡን መንግሥት የሚደግፉ ሕዝባዊ ሰልፎች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተካሂደዋል። በእነዚህ ሰልፎች ላይም መንግሥት ባለፉት ሥምንት ዓመታት ያመጣቸውን ለውጦች እና የተገኙ ስኬቶችን የሚያወሱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) ለሰጡት ስኬታማ አመራርነት የሚያሞግሱና የሚያመሠግኑ መልዕክቶች ተስተጋብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ቀኑን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሕዝባዊ ግፊትና ትግል ያመጣው የመጋቢት ለውጥ ኢትዮጵያን ወደ ኋላ ያስቀሩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ስብራቶችን መጠገን ያስቻሉ ሪፎርሞች የተተገበሩበት ነው ብለዋል። ለሕዝባችን የላቀ ተጠቃሚነት፣ ለሀገራችን ክብርና ብልፅግና መሳካት አበክረን እንሠራለን ሲሉም ገልጸዋል። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በበኩሉ ቀኑን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በኃይልና በምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ አስደማሚ ስኬቶችን አስመዝግባለች ብሏል። የለውጡን መሠረት ከማስፋትና ከማጽናት ወደ ማላቅ የተሸጋገረችው ኢትዮጵያ፤ በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌትነቷን በተግባር ታውጃለች ሲልም ገልጿል። ይህን ለውጥ ዕውን ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ፤ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በድል እንደሚያሳርጉት ጥርጥር የለውም ነው ያለው። • የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ስምምነት የኢትዮጵያ መንግሥት በInvest in Ethiopia 2026 ፎረም፤ ከቻይና፣ ፖላንድ፣ ሕንድ፣ ሲንጋፖር እና ኬንያ ከመጡ አጋሮች ጋር የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ታሪካዊ የኢንቨስትመንት ስምምነት መፈራረሙን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት አስታውቋል። በታዳሽ ኃይል፣ በማዕድንና በአረንጓዴ አሞኒያ ዘርፎች ላይ ያተኮሩት እነዚህ ስምምነቶች፤ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችን ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ጉልህ ማሳያ ናቸው ብሏል። በተመሳሳይ ጽሕፈት ቤቱ ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለውን የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ የሚተካ የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 ሆኖ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል ብሏል። የ1954 የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕጉ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየ በመሆኑ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግሥት እና ከወንጀል ፍትሕ ፖሊሲ እንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በዘርፉ ካሉ አዳዲስ አሠራሮችና የቴክኖሎጂ እድገቶች አኳያ ከዘመኑ ጋር በተጣጣመ መልኩ መከለሱ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ባለፉት ዓመታት የአዲስ ሕግ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል። ብዙ ምክክር ተደርጎበት የጸደቀው የሕግ መድብል አዳዲስ አሠራሮችን የሚያስተዋውቅ፤ የወንጀል ምርመራ፣ ክስና ማስረጃ ሥርዓቱን ወደአዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው ሲልም አስገንዝቧል ጽሕፈት ቤቱ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3889
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2648
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8441
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6928
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60867
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54863
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35364
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32981
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27980
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 27225
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26722
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26298
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60867
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54863
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35364
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32981
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 480
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ
Apr 12, 2026 974
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ በቀበኔሳ ገቢሳ ትንሣኤ ለሰው ልጅ ተስፋን፣ ዘለዓለማዊ ሕይወትን እና ከኃጢአት ነፃ መውጣትን የሚያበስር ኃይማኖታዊ በዓል ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ በመነሳቱ የሰው ልጅ የዘለዓለም የሕይወት አክሊልን ተስፋ ያደረገበት፣ የእግዚአብሔር ፍቅር የተገለጠበት እንዲሁም የሰው ልጅ ከዘለዓለም ሞትና ከኃጢአት ባርነት ነፃ የወጣበት የድኅነት፣ የፍቅር፣ የጽናትና የተስፋ ብርሃን ብስራት ነው፡፡ የትንሣኤ በዓል ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የመነሳቱ ታላቅ ምሥጢር የሚታሰብበት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንስ የሰው ልጅ ከውርደት ወደ ክብር፣ ከኃጢያት ባርነት ወደ ድኅነት እንዲሁም ከጉስቁልና ወደ ብሩህ ተስፋ የተሸጋገረበት የድል አዋጅ ነው። በዕለቱም በሞት ላይ ሕይወት፣ በሐዘን ላይ ደስታ፣ በቂም ላይ ይቅርታ ተበስሮበታል። ከበዓላት ሁሉ የላቀ የነጻነት ተምሳሌት ነው ትንሣኤ። 👉የትንሣኤ ሕያው አስተምሮ በዕለት ተዕለት ሕይወት ትንሣኤ ሲከበር ከሥርዓተ አምልኮ ባለፈ፣ በዓሉ የሚሰጠውን ታላቅ አስተምሮ ማጤን ይገባል። ትንሣኤ በየቀኑ ካለንበት ድካምና ውድቀት በአዲስ መንፈስ የመነሳት አቅም ነው። በዓሉ የሚያስተምረንን የጽናት፣ የተስፋና የአብሮነት ዕሴት በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ መኖር ያስፈልጋል። ለዚህም የተቸገሩን መርዳት፣ የታመሙትን መጠየቅና የተጣሉትን ማስታረቅ የበዓሉን ትርጉም እውነተኛ ያደርገዋል። 👉የኢትዮጵያ ትንሣኤ፤ በፈተና የጸና ብርሃን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዓሉን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት፤ "የዘንድሮውን የትንሣኤ በዓል የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በፈታኝ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ሆና እያለች ነው። መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችንም እሾህ የበዛበት ሊሆን ይችላል። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ፣ በጨለማ ወጥመድ ሊያሥሩን የሚሞክሩ መሰናክሎች ቢበዙም፣ እምነታችን ግን ከሕማማት በኋላ ትንሣኤ እንደሚመጣ ነው" ብለዋል፡፡ "ኢትዮጵያ ዛሬም ትንሳኤዋን እያየች ነው። መቃብሯ ተከፍቷል፤ ማኅተሙም ተሰብሯል። የትንሣኤውን ዜና ሊያደበዝዙ የሚሞክሩ የውሸት ወሬዎችና ተስፋ አስቆራጭ ትረካዎች የሀገራችንን የብርሃን ጉዞ ሊገቱት አይችሉም። ትንሳኤው እውነት ነው፤ ብርሃኑም የማይቀለበስ ሀቅ ሆኗል" ሲሉም አረጋግጠዋል፡፡ 👉ዴሞክራሲ እና ብሔራዊ ምክክር፤ የተስፋ ምዕራፎች የኢትዮጵያ ትንሣኤ አንዱ መገለጫ ዴሞክራሲን የመገንባት ጽናት ነው። ትንሣኤ ያለ ሕማማት እንደማይገኝ ሁሉ ዴሞክራሲ ያለ ፈተና በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ዴሞክራሲ የሚገነባው በጽናት እንጂ በፍርሃት አይደለም። ዴሞክራሲን እየገነባን በትዕግሥትና በቆራጥነት ወደ ተስፋዋ ምድር እንደርሳለን። አሁን ያለው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጦርነት፣ የኢኮኖሚ ቀውስና ማህበራዊ አለመረጋጋት የትንሳኤን ትምህርት ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊ ያደርገዋል፡፡ ችግሮችን በብቸኝነት የምንወጣበት ጊዜ አብቅቷል። ዛሬ እንደህዝብ የሚያስፈልገን ከ"እኔ" ወደ "እኛ" መሸጋገር፣ የግል ፍላጎትን ለጋራ ስኬት መስዋዕት ማድረግ ግድ የሚልበት ወቅት ላይ ነን። የአንድነት ጉዟችንን በማጠናከር ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ጫናዎችን ለመቋቋም በጋራ መቆም ይገባናል። የተቸገሩትን በመርዳት፣ የታመሙትን በመጠየቅና የተጣሉትን በማስታረቅ የተግባር አብሮነትን በማሳየት የበዓሉን እውነተኛ ትርጉም መግለጥ ይገባል፡፡ 👉ምርጫ፤ ከኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበትና ተስፋ የታደሰበት ዕለት ነው። እኛም በምርጫ ካርዳችን የሃሳብ ልዩነትን በዴሞክራሲያዊ አንድነት ድል በማድረግ የኢትዮጵያን የብልፅግና ትንሳኤ እናረጋግጣለን። በትንሣኤ በዓል የምንማረው ይቅርታና ጽናትም ለምርጫችን ስኬት አቅም ይሆናል። በኅብረት የምንሰጠው ድምፅም የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ የመቅረጽ ኃይል በእጃችን መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው "ምርጫ የኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ነው። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም። በዓለም ላይ በደልዳላ መንገድ ተጉዞ ዴሞክራሲን የገነባ ሀገር የለም። ዴሞክራሲና ብልፅግና ያለ ጽናት አይሳኩም። ከእኛ በፊት ዐመጻውን በትዕግሥት የመከቱ ተሻግረዋል፤ ሑካታውን በጽናት ያለፉ አሳክተዋል። ብንመኝም ፈተናውን አናስቀርም፤ መጽናት ግን እንችላለን። ከድኅነት መውጫው ብርታታችን፣ ወደ ዴሞክራሲ መድረሻችው ትዕግሥታችን እንደሆነ አምነን ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በሙሉ ልባችን እንትጋ!!" ብለዋል። 👉የወደፊት እጣ ፈንታችን በእጃችን ከፊታችን የሚጠብቁን ሀገራዊ ምክክርና የ2018 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የወደፊት መጻኢ ዕድል የሚወስኑ ታላላቅ ሁነቶች ናቸው። እነዚህ ሂደቶች ስኬታማ የሚሆኑት እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን ሲወጣ ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በልባችን ውስጥ ይቅርታና አብሮነት ሲነግስ ብቻ ግቡን ይመታል። ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበት እንደሆነው ሁሉ፣ በምክክሩም ጥልን፣ ጥርጣሬን፣ ያለመግባባት መንፈስን ድል መንሳት ይገባል፤ ቅንነት፣ ተስፋና መተሳሰብ ለምክክሩ ስኬት የመተማመኛ ቁልፎች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ 2018 ዓ.ም ደግሞ የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ ማሳያ አንጓ ነው፤ የዜጎች ነፃ ተሳትፎ መብታቸውን የሚያስከብሩበት ፍላጎታቸውን የሚያረጋግጡበት ማረጋገጫ ማህተም ጭምር፡፡ ዜጎች የመምረጥና የመመረጥ መብታቸውን የሚያስከብሩበት፤ የሌላውን ሃሳብ አክብረው የራሳቸውን የሚያስከብሩበት ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በጋራ የሚቆሙበት መድረክ ነው፡፡ ትንሣኤ የድልና የነጻነት በዓል ነው። ይህንን ታላቅ ዕለት ስናከብር ያለፈውን ቁስል ሽረን፣ ለነገ ተስፋ ሰንቀን መሆን አለበት። እርስ በእርስ በመደጋገፍ፣ ችግሮችን በንግግር በመፍታት ለሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ስኬታማነት የድርሻችንን መወጣት ይገባናል። የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ እንቁም! መልካም የትንሳኤ በዓል!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም