ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የብዝሃ-ዘርፍ የኢኮኖሚ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን መደላድል ፈጥሯል
Nov 24, 2025 35
ድሬደዋ፣ ህዳር 15/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ የብዝሃ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ጉዞ እንዲሳካ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ተናገሩ። ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ዛሬ ድሬ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የስራ እንቅስቃሴን ተመልክተዋል። ኮሚሽነሩ በወቅቱ እንዳሉት፤ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ የዘመናት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እየፈታ ይገኛል። ከወረቀትና ከሰው ንክኪ የፀዱ አገልግሎቶች ተደራሽ መደረጋቸው ደግሞ ብልሹ አሠራሮችንና የሙስና ተግባራትን እንደሚቀንሱ ገልጸዋል። ይበልጡኑ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎቶች ተደራሽ መሆናቸው እንደ አገር ለተጀመሩ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ ግስጋሴዎች ዳር መድረስ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል። በድሬደዋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዚሁ ጅምር ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፥ የተጀመረውን ስራ ለማሳደግ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ፥ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በስፋትና በጥራት በመላው አገሪቷ ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል። የድሬደዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሐይር ሐጂ ኑር በበኩላቸው፥ በድሬ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት 10 ተቋማት 28 አገልግሎቶችን በጥራትና በፍጥነት ለተገልጋዮች ተደራሽ እያደረጉ መሆኑን አንስተዋል። ባለፉት ሁለት ወራት ከአራት ሺህ በላይ ለሚሆኑ ነዋሪዎች የተቀናጀ አገልግሎት መሰጠቱን ጠቅሰው፥ የተጀመረውን ስራ ለማስፋትና ለማሳደግ ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል። የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ዛሬ ረፋድ ላይ በድሬዳዋ ከተማ የተገነባውን የመጀመሪያ ምዕራፍ የኮሪደር ልማትንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በመዲናዋ ለአምራቾች በተሰጠው ትኩረት በምርታማነትና በገበያ ማረጋጋት ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል
Nov 24, 2025 31
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018(ኢዜአ)፡- በመዲናዋ አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርታማነትን በማሳደግ የገበያ ማረጋጋት ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ በተሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ለውጦች መገኘታቸውን የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር ገለጹ። 20ኛውን የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የተዘጋጀው ከተማ አቀፍ ኤግዚቢሺንና ባዛር ተከፍቷል። ለተከታታይ ሦስት ቀናት በሚቆየው በዚሁ ኤግዚቢሽንና ባዛር ገበያን የሚያረጋጉ የተለያዩ ምርቶች ቀርበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የለውጡ መንግሥት ህብረ-ብሄራዊ ፌደራሊዝምን የማጠናከርና ቀድሞ የነበሩ ጉድለቶችን የማረም ስራ ሰርቷል። ይህም ዜጎች ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር አካባቢያቸውን ይበልጥ እንዲያለሙ ትልቅ እድል ፈጥሯል ብለዋል። በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛር ኢንዱስትሪዎች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ ተሞክሮና ልምድ እንዲለዋወጡ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል። በራስ ምርት የመጠቀምና የመኩራት ባህል እንዲጎለብት እንዲሁም የኢትዮጵያን እንግዛ ንቅናቄን የበለጠ ውጤታማ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል። በኤግዚቢሽንና ባዛሩ የቀረቡ ምርቶች የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ትግበራ ፍሬ እያፈራ እንደሚገኝ የሚያመላክቱ፣ ገበያን የሚያረጋጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በመዲናዋ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት በተጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰው፥ ኢንዱስትሪዎቹ ለበርካቶች የስራ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል። ከተማ አስተዳደሩ የምርትና አገልግሎት ማሳያ፣መሸጫና የገበያ ትስስር መፍጠሪያ መድረኮችን በማስፋት ለኢንዱስትሪዎች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ፀጋዬ ደበሌ በበኩላቸው፥ በኤግዚቢሽንና ባዛሩ 130 የሚሆኑ አምራቾች ምርታቸውን የሚያቀርቡ መሆኑን ገልጸዋል። ኢንዱስትሪዎች፣ በከተማ ግብርና የተሰማሩ አምራቾችና ሸማች ህብረት ስራ ማህበራት የተሳተፉበት ኤግዚቢሽንና ባዛሩ ሸማቾችና አምራቾችን ቀጥታ በማገናኘት የዋጋ ንረትን መከላከልን ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። በኤግዚቢሽንና ባዛሩ የተሳተፉ አምራቾች በሰጡት አስተያየት፥ የተለያዩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረባቸውን ተናግረዋል። ከኤግዚቢሽንና ባዛሩ በተጓዳኝ የደም ልገሳ መርሃ ግብርም ተካሂዷል።
አገልግሎቱ ለስደተኞችና ተመላሾች እየሰጠ ያለውን አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠል አለበት
Nov 24, 2025 29
አዲስ አበባ፤ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ለስደተኞችና ተመላሾች እየሰጠ ያለውን አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ። ቋሚ ኮሚቴው የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎትን የ2018 ዓ.ም የአንደኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።   የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ኃላፊ ጠይባ ሀሰን የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት፥ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከ34 ሀገራት የመጡ ከአንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን በ27 መጠለያዎች ውስጥ እንደምታስተናግድ ገልጸዋል። ተቋሙ የስደተኞችን አገልግሎት አሰጣጥ እና ደኅንነት ጥበቃ ሥራ ማጎልበት ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ባለፉት ሶስት ወራት እውቅና መስጠትና ምዝገባ፣ ዶክመንቴሽን፣ የደኅንነት ስጋትን መቀነስና ዘላቂ መፍትሄ ላይ አበረታች ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል። በተጨማሪም የጤና እና ትምህርት አገልግሎት ተደራሽነትን በማሳደግ፣ ለስደተኞች እና ተቀባይ ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ፈጠራና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን አስታውቀዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር)፤ አገልግሎቱ ለበርካታ ስደተኞች እየሰጠ ያለው አገልግሎት አበረታች መሆኑን ተናግረዋል።   በቀጣይም የሀገሪቱን ሠላምና ደኅንነት ባረጋገጠ መልኩ አገልግሎቱን ከሚመለከታቸው አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት አገልግሎቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አገልግሎቱ እየሰራ ያለውን ስራዎች አድንቀው፥ በቀጣይ በሀገሪቱ ላይ ጫናዎች እንዳይፈጠሩ ትኩረት አድርጎ መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። እንዲሁም በማህበራዊ አገልግሎት በሆኑ የጤናና ትምህርት አገልግሎቶች ላይ ጫናዎች እንዳይፈጠሩ ትኩረት ማድረግ ይገባል ነው ያሉት። ምክር ቤቱም አገልግሎቱ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አፍሪካ በአውሮፓ ገበያ ያላትን ተደራሽነት ለማሳደግ ታሪፍ እና ታሪፍ ያልሆኑ ገደቦች ሊነሱ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Nov 24, 2025 39
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 15/2018 (ኢዜአ)፡- አፍሪካ በአውሮፓ ገበያ ውስጥ ያላት ድርሻ እና ተደራሽነት እንዲጨምር ታሪፍና ታሪፍ ያልሆኑ ገደቦች መነሳት እንደሚገባቸው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሰባተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ በአንጎላ ሉዋንዳ ተጀምሯል። ጉባኤውን የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾና የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት አንቶኒዮ ኮስታ በጋራ መርተውታል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ የህብረቱ ሀገራት መሪዎች፣ የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን እና ሌሎች የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ ወጣቶች፣ የሲቪክ ማህበራት እና የንግድ ልዑካን በጉባኤው ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ። ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር አፍሪካ በቅርቡ የዓለም እድገት ኃይል ምንጭ እንደምትሆን ገልጸዋል። የተትረፈረፈ የገበያ እድል፣ የሰው ኃይል እና የተፈጥሮ ሀብቶች የዓለም እድገት ዋንኛ ተዋናይ የሚያደርጓት አቅሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ሊቀ መንበሩ በአፍሪካ እና በአውሮፓ መካከል ሚዛናዊ የሆነ የንግድ አጋርነት ሊኖር እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በአፍሪካ ያለው የአውሮፓ ኢንቨስትመንት መጨመር እንዳለበትም አንስተዋል። አፍሪካ ሀገራት ወደ አውሮፓ ህብረት ገበያ በሚፈለገው መጠን እንዳይገቡ ያደረጋቸው የታሪፍ እና ከታሪፍ ጋር ያልተያያዙ ገደቦች እንዲነሱም ጠይቀዋል። እኩልነት እና የጋራ ፍላጎቶችን መሰረት ባደረገ መልኩ ጠንካራ የባለብዙወገን ትብብር መገንባት እንደሚገባ አሳስበዋል። ሰላም፣ ደህንነት፣ የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት፣ ፍልሰት እና የሰዎች እንቅስቃሴና የሰው ኃይል ልማት መሪዎቹ ውይይት ከሚያደርጉባቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የተቋማቱ መሪዎች ለባለብዙ ወገን ትብብር፣ አጋርነት እና እየታዩ ላሉ ፈተናዎች የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የሚወያዩባቸው ጉዳዮች በአጀንዳ 2063፣ በዘላቂ የልማት ግቦች እና የአፍሪካ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት የ2030 የጋራ ራዕይ ጋር የተቆራኙ መሆናቸውም ተመላክቷል። ከዋናው የመሪዎች ጉባኤ አስቀድሞ የወጣቶች እና የሲቪክ እንዲሁም የንግድ ፎረሞች መካሄዳቸው ይታወቃል። ሰባተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እስገ ነገ ይቆያል።
የሚታይ
አፍሪካ በአውሮፓ ገበያ ያላትን ተደራሽነት ለማሳደግ ታሪፍ እና ታሪፍ ያልሆኑ ገደቦች ሊነሱ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Nov 24, 2025 39
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 15/2018 (ኢዜአ)፡- አፍሪካ በአውሮፓ ገበያ ውስጥ ያላት ድርሻ እና ተደራሽነት እንዲጨምር ታሪፍና ታሪፍ ያልሆኑ ገደቦች መነሳት እንደሚገባቸው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሰባተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ በአንጎላ ሉዋንዳ ተጀምሯል። ጉባኤውን የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾና የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት አንቶኒዮ ኮስታ በጋራ መርተውታል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ የህብረቱ ሀገራት መሪዎች፣ የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን እና ሌሎች የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ ወጣቶች፣ የሲቪክ ማህበራት እና የንግድ ልዑካን በጉባኤው ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ። ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር አፍሪካ በቅርቡ የዓለም እድገት ኃይል ምንጭ እንደምትሆን ገልጸዋል። የተትረፈረፈ የገበያ እድል፣ የሰው ኃይል እና የተፈጥሮ ሀብቶች የዓለም እድገት ዋንኛ ተዋናይ የሚያደርጓት አቅሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ሊቀ መንበሩ በአፍሪካ እና በአውሮፓ መካከል ሚዛናዊ የሆነ የንግድ አጋርነት ሊኖር እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በአፍሪካ ያለው የአውሮፓ ኢንቨስትመንት መጨመር እንዳለበትም አንስተዋል። አፍሪካ ሀገራት ወደ አውሮፓ ህብረት ገበያ በሚፈለገው መጠን እንዳይገቡ ያደረጋቸው የታሪፍ እና ከታሪፍ ጋር ያልተያያዙ ገደቦች እንዲነሱም ጠይቀዋል። እኩልነት እና የጋራ ፍላጎቶችን መሰረት ባደረገ መልኩ ጠንካራ የባለብዙወገን ትብብር መገንባት እንደሚገባ አሳስበዋል። ሰላም፣ ደህንነት፣ የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት፣ ፍልሰት እና የሰዎች እንቅስቃሴና የሰው ኃይል ልማት መሪዎቹ ውይይት ከሚያደርጉባቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የተቋማቱ መሪዎች ለባለብዙ ወገን ትብብር፣ አጋርነት እና እየታዩ ላሉ ፈተናዎች የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የሚወያዩባቸው ጉዳዮች በአጀንዳ 2063፣ በዘላቂ የልማት ግቦች እና የአፍሪካ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት የ2030 የጋራ ራዕይ ጋር የተቆራኙ መሆናቸውም ተመላክቷል። ከዋናው የመሪዎች ጉባኤ አስቀድሞ የወጣቶች እና የሲቪክ እንዲሁም የንግድ ፎረሞች መካሄዳቸው ይታወቃል። ሰባተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እስገ ነገ ይቆያል።
የኢትዮጵያ የቡድን 20 መሪዎች ጉባኤ ተሳትፎ በዓለም የባለብዙወገን መድረኮች እያደገ የሚገኘውን ሚናዋን በግልጽ ያሳየ ነው
Nov 24, 2025 98
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ያደረገችው ተሳትፎ በዓለም የባለብዙወገን መድረኮች እያደገ የመጣውን የዲፕሎማሲ ሚና በግልጽ የታየበት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ። የቡድን 20 አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ተካሄዷል። ጉባኤው በአፍሪካ የተካሄደው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመሪዎች ጉባኤ ላይ ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተሳተፉበት የቡድን 20 ጉባኤ እና የጎንዮሽ ውይይቶችን አስመልክቶ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በማብራሪያቸው ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ ጋባዥነት በጉባኤው ላይ መሳተፏን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጉባኤው ጎን ለጎን ከበርካታ ሀገራት መሪዎች እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጉባኤው አዘጋጅ ሀገር ደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ስሪል ራማፎሳ ጋር መወያየታቸውንና ውይይቱ በጉባኤው የአፍሪካን የጋራ ድምጽ እና ፍላጎት ማሰማትና ማንጸባረቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ እንደነበር አውስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከአቡዳቢ አልጋ ወራሽ ሼክ ካሌድ ቢን መሐሙድ ቢን ዛይድ አል ናህያን፣ ከፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታመር፣ ከኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዲክ ሾፍ እና ከሌሎች ሀገራት መሪዎች ጋር መምከራቸውን አመልክተዋል። ከእስያ ሀገራትም መካከል ከቪዬተናም፣ ኮሪያ ሪፐብሊክ እና ኢንዶኔዥያ መሪዎች ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። በባለብዙ ወገን መድረክም ከተባበሩት መንግስት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ ከአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ፣ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ እና ከዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ ጋር መምከራቸውንም እንዲሁ። በአፍሪካ ደረጃም ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሲድ ኡልድ ታህ ጋር መወያየታቸውን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በባለብዙ ወገን መድረክ እያደገ ያለውን ቁመና በማንሳት የበለጠ ትብብሮችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር መደረጉን ነው ፕሬስ ሴክሬተሪያቷ ያብራሩት። በሌላ በኩል በውይይቶቹ ኢትዮጵያ እያደረገች የምትገኘው የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ያስገኟቸው አመርቂ ውጤቶች እና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች እንዲሁም የኢኮኖሚ ማረጋጋት ተግባራት መነሳታቸውን ገልጸዋል። ሀገራትና ተቋማቱ ማሻሻያዎቹን እንዲደግፉም ጥሪ መቅረቡን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ እያደገ የመጣው ሚናዋ ሌላኛው የውይይቶቹ ትኩረት ነበር። ፕሬስ ሴክሬተሪያቷ ኢትዮጵያ በቅርቡ 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧን አውስተው፤ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድና ሁሉን አካታች እንዲሆን አጋሮች ድጋፍ በሚያደርጉበትና ኢትዮጵያ ልምድ በመቅሰም በምትችልበት ሁኔታ ላይ ውይይቶች መደረጋቸውን አመልክተዋል። ጉባኤው በሺዎች የሚቆጠሩ የሚሳተፉበት በመሆኑ ለቱሪዝም ልማት፣ ለመሰረተ ልማት ግንባታ እና ኢኮኖሚ እድገት ጉልህ አበርክቶ እንደሚኖረው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ላይ ንግግር ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎን በተካሄደው የኮምፓክት ፎር አፍሪካ ስብሰባ ላይ በመሳተፍ ባደረጉት ንግግር የበለጸጉ ሀገራት ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ፍላጎቶች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸውን አብራርተዋል። በአጠቃላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ውጤታማ እና ፍሬያማ ተሳትፎ ማድረጋቸውን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ የጉባኤው ተሳትፎ በዓለም የባለብዙወገን መድረኮች ላይ ያላት ቁመና የበለጠ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ኢትዮዽያ በሀገራዊ ሪፎርሙ ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው
Nov 24, 2025 141
አዲስ አበባ፤ ህዳር 15/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮዽያ በሀገራዊ ሪፎርሙ ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሀላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለፁ። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች ጋር ተወያይተዋል። አቶ አደም በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች ዘመናትን የተሻገረ ጠንካራ ግንኙነት አላቸው። ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ ትልቅ የልማት አጋር መሆኗን ጠቁመው የኢትዮጵያ የልማት እና የሪፎርም አጀንዳ እንዲሳካ ዩናይትድ ኪንግደም ለምትሰጠው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል። ሀገራቱ በየዘርፉ ያላቸው ጥልቅ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከር ብልፅግና ፓርቲ የሚጠበቅበትን ሚና እንደሚያጠናክርም አረጋግጠዋል። በትምህርት እና በጤና ዘርፍ ያላቸው አጋርነት ውጤታማ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ስኬታማ ትብብር በሌሎች ዘርፎችም ለማስፋት ቁርጠኛ ነን ብለዋል። በብልፅግና ፓርቲ አመራር ሰጪነት በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህን ስኬቶች ለማስቀጠል የሚደረገው ርብርብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ብልፅግና ፓርቲ ለተቋም ግንባታ ሥራዎች ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እና ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ ነጻ ገለልተኛ ተቋማት እውን መሆን ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል። የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ረገድም ፓርቲው ትልልቅ እርምጃዎችን መውሰዱን ገልጸው፤ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት በመንግሥት ካቢኔ እንዲካተቱ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል። ቀጣዩ ምርጫ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው፤ ምርጫው የህዝብ ተሳትፎ የተረጋገጠበት ተአማኒ እንዲሆን ብልፅግና ፓርቲ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር እና የአፍሪካ ኀብረት ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ዳረን ዌልች በበኩላቸው ኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ እና ምሳሌ የሚሆን ግንኙነት ያላቸው መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም በትክክለኛ መንገድ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በተሻለ ደረጃ እንደሚቀጥል አምናለሁ ብለዋል። ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ የተቋም ግንባታ ሥራዎችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን አምባሳደሩ አረጋግጠዋል።
ዝቅተኛ በካይ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል ርብርብ እየተደረገ ነው
Nov 24, 2025 122
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፡- በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ዝቅተኛ በካይ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስቴሩ ከፓወር አፍሪካ ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀው ሁለተኛው ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኤግዚቢሽንና ባዛር ከታኅሣሥ 9 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ያካሂዳል፡፡ ሚኒስትሩ አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ሁለተኛውን ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኤግዚቢሽንና ባዛር ለማካሄድ በተደረጉ ዝግጅቶችና በሚጠበቁ ውጤቶች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።   ሚኒስትር አለሙ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት መተግበር የጀመረው አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ መደላድል እየፈጠረ ነው። የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ሥራዎች ኢትዮጵያ ኮፕ 32 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እንድታስተናግድ እንድትመረጥ አድርጓታል ሲሉም ጠቅሰዋል። በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍም ታዳሽ ኃይልም ሆነ ዝቅተኛ በካይ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ከታኅሣሥ 9 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚካሄደው ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ ኤግዚብሽንና ባዛር ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል።   በኤግዚቢሽን እና ባዛሩ ላይ ኤሌክትሪክን ጨምሮ የተለያዩ ታዳሽ ኃይል የሚጠቀሙ ተሽከርካሪ አምራቾች፣ ቴክኖሎጂ አቅራቢዎች፣ በዘርፉ የተሰማሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የጥናትና ምርምር ተቋማት እንደሚሳተፉ አብራርተዋል። በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችና መፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ በጋራ ውይይት የሚደረግበት መርሐ ግብር መሰናዳቱንም አመልክተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ለብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ታዳሚዎች መልካም መስተንግዶ ለመስጠት ተዘጋጅተናል -በሆሳዕና ከተማ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት
Nov 24, 2025 155
ሆሳዕና፤ ህዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን ለማክበር የሚመጡ እንግዶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ መዘጋጀታቸውን በሆሳዕና ከተማዋ የሚገኙ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ገለጹ። የከተማ አስተዳደሩ በበኩሉ በከተማዋ ለሚከበረው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን የተሟላ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል። የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ዘንድሮ ለ20ኛ ጊዜ "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሆሳዕና ከተማ ይከበራል፡፡ በሆሳዕና ከተማ በዓሉ መከበሩን አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዳሉት በዓሉን ለማክበር የሚመጡ እንግዶችን ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በተላበሰ መልኩ ለመቀበል ተዘጋጅተዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል የገብረፃዲቅ ሆቴልና ስፓ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብርሃም ሙሌ እንደገለፁት ለበዓሉ የሚመጡ እንግዶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። የእንግዶችን ምቾት የሚያስጠብቁ የሆቴል አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የአካባቢውን ወግና ባህል ለማስተዋወቅ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል፡፡ "ኢትዮጵያዊ እንግዳ ተቀባይነትን በሚያንጸባርቅ መልኩ መስተንግዶ ለመስጠትና ንፁህ የመኝታና የማረፊያ አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጅተናል" ሲሉም ነው የገለጹት። ሌላኛው የትንሳኤ ሆቴል ሥራ አስኪያጅ አቶ አስቻለው ብርሃኑ በበኩላቸው ሆቴሉ እንግዶችን በጥሩ መስተንግዶ በመቀበል ተደስተው እንዲመለሱ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ የሀዲያን ህዝብ ለክብር እንግዳ የሚያዘጋጀውን "አተካና" የተሰኘ ባህላዊ ምግብ ጨምሮ ሌሎች ባህላዊ ምግቦችን በማዘጋጀት እንግዶችን ለመቀበል የተሟላ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ከከተማው የታክሲ አሽከርካሪዎች መካከል ተመስገን ኢቲቦ ፤ ለበዓሉ ታዳሚዎች ከሚሰጡት የትራንስፖርት አገልግሎት ባለፈ የአካባቢውን የመዝናኛና የቱሪስት መስህቦች እንዲጎበኙ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። አቶ አማረ ገብረሃና የተባሉ የከተማው ነዋሪ በበኩላቸው ለብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የሚመጡ እንግዶችን በበጎ ፍቃደኝነት ለማገልገል መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ፤ በሃገር ደረጃ የሚከበረውን 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ባማረና በደመቀ መልኩ እንዲከበር አስትዳደሩ የተሟላ ዝግጅት ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ የተጀመሩ አዳዲስ መሰረተ ልማቶችን ከማጠናቀቅ ጀምሮ ነባሮቹም ለእንግዶች ተገቢውን አገልገሎት እንዲሰጡ የማዘጋጀት ሥራ ተከናውኗል ብለዋል፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የከተማዋን የቱሪስት መስህቦች እንዲጎበኙ የሚደረግበት ሁኔታ መመቻቸቱን ጠቅሰው፣ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም በኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንግዶችን ተቀበልው እንዲያስተናግዱ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡  
የኢትዮጵያ የቡድን 20 መሪዎች ጉባኤ ተሳትፎ በዓለም የባለብዙወገን መድረኮች እያደገ የሚገኘውን ሚናዋን በግልጽ ያሳየ ነው
Nov 24, 2025 98
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ያደረገችው ተሳትፎ በዓለም የባለብዙወገን መድረኮች እያደገ የመጣውን የዲፕሎማሲ ሚና በግልጽ የታየበት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ። የቡድን 20 አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ተካሄዷል። ጉባኤው በአፍሪካ የተካሄደው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመሪዎች ጉባኤ ላይ ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተሳተፉበት የቡድን 20 ጉባኤ እና የጎንዮሽ ውይይቶችን አስመልክቶ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በማብራሪያቸው ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ ጋባዥነት በጉባኤው ላይ መሳተፏን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጉባኤው ጎን ለጎን ከበርካታ ሀገራት መሪዎች እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጉባኤው አዘጋጅ ሀገር ደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ስሪል ራማፎሳ ጋር መወያየታቸውንና ውይይቱ በጉባኤው የአፍሪካን የጋራ ድምጽ እና ፍላጎት ማሰማትና ማንጸባረቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ እንደነበር አውስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከአቡዳቢ አልጋ ወራሽ ሼክ ካሌድ ቢን መሐሙድ ቢን ዛይድ አል ናህያን፣ ከፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታመር፣ ከኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዲክ ሾፍ እና ከሌሎች ሀገራት መሪዎች ጋር መምከራቸውን አመልክተዋል። ከእስያ ሀገራትም መካከል ከቪዬተናም፣ ኮሪያ ሪፐብሊክ እና ኢንዶኔዥያ መሪዎች ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። በባለብዙ ወገን መድረክም ከተባበሩት መንግስት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ ከአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ፣ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ እና ከዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ ጋር መምከራቸውንም እንዲሁ። በአፍሪካ ደረጃም ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሲድ ኡልድ ታህ ጋር መወያየታቸውን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በባለብዙ ወገን መድረክ እያደገ ያለውን ቁመና በማንሳት የበለጠ ትብብሮችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር መደረጉን ነው ፕሬስ ሴክሬተሪያቷ ያብራሩት። በሌላ በኩል በውይይቶቹ ኢትዮጵያ እያደረገች የምትገኘው የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ያስገኟቸው አመርቂ ውጤቶች እና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች እንዲሁም የኢኮኖሚ ማረጋጋት ተግባራት መነሳታቸውን ገልጸዋል። ሀገራትና ተቋማቱ ማሻሻያዎቹን እንዲደግፉም ጥሪ መቅረቡን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ እያደገ የመጣው ሚናዋ ሌላኛው የውይይቶቹ ትኩረት ነበር። ፕሬስ ሴክሬተሪያቷ ኢትዮጵያ በቅርቡ 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧን አውስተው፤ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድና ሁሉን አካታች እንዲሆን አጋሮች ድጋፍ በሚያደርጉበትና ኢትዮጵያ ልምድ በመቅሰም በምትችልበት ሁኔታ ላይ ውይይቶች መደረጋቸውን አመልክተዋል። ጉባኤው በሺዎች የሚቆጠሩ የሚሳተፉበት በመሆኑ ለቱሪዝም ልማት፣ ለመሰረተ ልማት ግንባታ እና ኢኮኖሚ እድገት ጉልህ አበርክቶ እንደሚኖረው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ላይ ንግግር ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎን በተካሄደው የኮምፓክት ፎር አፍሪካ ስብሰባ ላይ በመሳተፍ ባደረጉት ንግግር የበለጸጉ ሀገራት ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ፍላጎቶች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸውን አብራርተዋል። በአጠቃላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ውጤታማ እና ፍሬያማ ተሳትፎ ማድረጋቸውን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ የጉባኤው ተሳትፎ በዓለም የባለብዙወገን መድረኮች ላይ ያላት ቁመና የበለጠ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ኢትዮዽያ በሀገራዊ ሪፎርሙ ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው
Nov 24, 2025 141
አዲስ አበባ፤ ህዳር 15/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮዽያ በሀገራዊ ሪፎርሙ ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሀላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለፁ። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች ጋር ተወያይተዋል። አቶ አደም በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች ዘመናትን የተሻገረ ጠንካራ ግንኙነት አላቸው። ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ ትልቅ የልማት አጋር መሆኗን ጠቁመው የኢትዮጵያ የልማት እና የሪፎርም አጀንዳ እንዲሳካ ዩናይትድ ኪንግደም ለምትሰጠው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል። ሀገራቱ በየዘርፉ ያላቸው ጥልቅ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከር ብልፅግና ፓርቲ የሚጠበቅበትን ሚና እንደሚያጠናክርም አረጋግጠዋል። በትምህርት እና በጤና ዘርፍ ያላቸው አጋርነት ውጤታማ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ስኬታማ ትብብር በሌሎች ዘርፎችም ለማስፋት ቁርጠኛ ነን ብለዋል። በብልፅግና ፓርቲ አመራር ሰጪነት በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህን ስኬቶች ለማስቀጠል የሚደረገው ርብርብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ብልፅግና ፓርቲ ለተቋም ግንባታ ሥራዎች ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እና ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ ነጻ ገለልተኛ ተቋማት እውን መሆን ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል። የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ረገድም ፓርቲው ትልልቅ እርምጃዎችን መውሰዱን ገልጸው፤ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት በመንግሥት ካቢኔ እንዲካተቱ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል። ቀጣዩ ምርጫ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው፤ ምርጫው የህዝብ ተሳትፎ የተረጋገጠበት ተአማኒ እንዲሆን ብልፅግና ፓርቲ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር እና የአፍሪካ ኀብረት ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ዳረን ዌልች በበኩላቸው ኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ እና ምሳሌ የሚሆን ግንኙነት ያላቸው መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም በትክክለኛ መንገድ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በተሻለ ደረጃ እንደሚቀጥል አምናለሁ ብለዋል። ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ የተቋም ግንባታ ሥራዎችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን አምባሳደሩ አረጋግጠዋል።
ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር ትሰራለች 
Nov 24, 2025 125
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018(ኢዜአ)፦ ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ የፖለቲካ ቢሮ አባል እና የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ገለጹ። ኢትዮጵያ እና ቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩበት 55ኛ ዓመት ይከበራል። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ የሀገራቱን 55ኛ ዓመት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አስመልክቶ የደስታ መግለጫ መልዕክት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) አስተላልፈዋል። ዋንግ ዪ በመልዕክታቸው ቻይና እና ኢትዮጵያ ጥልቅ እና ለረጅም ጊዜ የቆየ ወዳጅነት እንዳላቸው ገልጸው ግንኙነታቸው በዓመታት መካከል ፀንቶ መቀጠሉን አመልክተዋል። ባለፉት 55 ዓመታት ሁለቱ ሀገራት የነበራቸው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በመልካም እምነት ላይ እና በአስፈላጊ ጊዜ እርስ በእርስ በመደጋገፍ ላይ የተመሰረተ መሆኑንም አመልክተዋል። ወዳጅነቱ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት አጋርነትና ትብብር ማሳያ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራቱ መሪዎች ስትራቴጂካዊ መሪነት የሁለትዮሽ ትብብሩ የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱንም ነው ያመለከቱት። ከምንጊዜውም በላይ የዳበረው የፖለቲካ የጋራ መተማመንና ፍሬያማ ተግባራዊ ትብብር መገለጫው የሆነው የሁለትዮሽ ግንኙነት ለሀገራቱ ህዝቦች ተጨባጭ ውጤቶችን ማስገኘቱን አብራርተዋል። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የ55ኛ ዓመቱን የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በዓል እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የቻይና አፍሪካ ትብብር ፎረም(ፎካክ) ጉባኤ ውጤቶችና የሀገራቱ መሪዎች የጋራ መግባባት ላይ የደረሱባቸውን ጉዳዮች ለመተግበር እንዲሁም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) የበለጠ ለማጠናከር ጥረት እንደሚያደርጉም አስታውቀዋል። በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የጋራ ራዕይን ማዕከል ያደረገ የቻይና-አፍሪካ ማህበረሰብ አዲስ የትብብር ምዕራፍ በመክፈቱ ላይ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1970 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ
የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ሎውረንስ ዎንግ ለይፋዊ ስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ
Nov 23, 2025 203
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 14/2018 (ኢዜአ)፦ የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ሎውረንስ ዎንግ ለይፋዊ ስራ ጉብኝት ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ለሚያደርጉት ይፋዊ ጉብኝት ዛሬ ማታ አዲስ አበባ ሲገቡ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቀባበል እንዳደረጉላቸው ገልጸዋል። ይህ ጉብኝት የሁለቱ ሀገራት አጋርነትን ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ ሲሆን፣ ተጨማሪ አዳዲስ የትብብር እድሎችን ለመዳሰስም ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ ከእ.አ.አ 2024 አንስቶ አራተኛው የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ። በተጨማሪም ዎንግ የሲንጋፖር የፋይናንስ ሚኒስትር ሲሆኑ ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 የሲንጋፖር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ሰርተዋል። ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1969 ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እ.አ.አ ጁን 2024 በሲንጋፖር ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ ከፕሬዝዳንት ታርማን ሻንሙጋራትናም እና ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ ጋር በሁለትዮሽ እና የባለብዙወገን ትብብር ዙሪያ ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ከሲንጋፖር ፕሬዝዳንት ጋር በኢስታና በፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ መለዋወጣቸውን ገልጸዋል። የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አማራጮችን ለመመልከት መስማማታቸውንም ተናግረዋል። የሀገራት መሪዎቹ የጉብኝት ልውውጥ በኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ያለውን ፍላጎት የሚያሳይ ነው። ሁለቱ ሀገራት በንግድና ኢንቨስትመንት፣ ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ቱሪዝም፣ ዘላቂ ልማት እና በሌሎች መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እየሰሩ ይገኛል።  
ፖለቲካ
ለብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል ታዳሚዎች መልካም መስተንግዶ ለመስጠት ተዘጋጅተናል -በሆሳዕና ከተማ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት
Nov 24, 2025 155
ሆሳዕና፤ ህዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን ለማክበር የሚመጡ እንግዶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ መዘጋጀታቸውን በሆሳዕና ከተማዋ የሚገኙ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ገለጹ። የከተማ አስተዳደሩ በበኩሉ በከተማዋ ለሚከበረው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን የተሟላ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል። የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ዘንድሮ ለ20ኛ ጊዜ "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሆሳዕና ከተማ ይከበራል፡፡ በሆሳዕና ከተማ በዓሉ መከበሩን አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዳሉት በዓሉን ለማክበር የሚመጡ እንግዶችን ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በተላበሰ መልኩ ለመቀበል ተዘጋጅተዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል የገብረፃዲቅ ሆቴልና ስፓ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብርሃም ሙሌ እንደገለፁት ለበዓሉ የሚመጡ እንግዶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። የእንግዶችን ምቾት የሚያስጠብቁ የሆቴል አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የአካባቢውን ወግና ባህል ለማስተዋወቅ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል፡፡ "ኢትዮጵያዊ እንግዳ ተቀባይነትን በሚያንጸባርቅ መልኩ መስተንግዶ ለመስጠትና ንፁህ የመኝታና የማረፊያ አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጅተናል" ሲሉም ነው የገለጹት። ሌላኛው የትንሳኤ ሆቴል ሥራ አስኪያጅ አቶ አስቻለው ብርሃኑ በበኩላቸው ሆቴሉ እንግዶችን በጥሩ መስተንግዶ በመቀበል ተደስተው እንዲመለሱ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ የሀዲያን ህዝብ ለክብር እንግዳ የሚያዘጋጀውን "አተካና" የተሰኘ ባህላዊ ምግብ ጨምሮ ሌሎች ባህላዊ ምግቦችን በማዘጋጀት እንግዶችን ለመቀበል የተሟላ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ከከተማው የታክሲ አሽከርካሪዎች መካከል ተመስገን ኢቲቦ ፤ ለበዓሉ ታዳሚዎች ከሚሰጡት የትራንስፖርት አገልግሎት ባለፈ የአካባቢውን የመዝናኛና የቱሪስት መስህቦች እንዲጎበኙ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። አቶ አማረ ገብረሃና የተባሉ የከተማው ነዋሪ በበኩላቸው ለብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የሚመጡ እንግዶችን በበጎ ፍቃደኝነት ለማገልገል መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ፤ በሃገር ደረጃ የሚከበረውን 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ባማረና በደመቀ መልኩ እንዲከበር አስትዳደሩ የተሟላ ዝግጅት ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ የተጀመሩ አዳዲስ መሰረተ ልማቶችን ከማጠናቀቅ ጀምሮ ነባሮቹም ለእንግዶች ተገቢውን አገልገሎት እንዲሰጡ የማዘጋጀት ሥራ ተከናውኗል ብለዋል፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የከተማዋን የቱሪስት መስህቦች እንዲጎበኙ የሚደረግበት ሁኔታ መመቻቸቱን ጠቅሰው፣ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም በኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንግዶችን ተቀበልው እንዲያስተናግዱ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡  
የኢትዮጵያ የቡድን 20 መሪዎች ጉባኤ ተሳትፎ በዓለም የባለብዙወገን መድረኮች እያደገ የሚገኘውን ሚናዋን በግልጽ ያሳየ ነው
Nov 24, 2025 98
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ያደረገችው ተሳትፎ በዓለም የባለብዙወገን መድረኮች እያደገ የመጣውን የዲፕሎማሲ ሚና በግልጽ የታየበት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ። የቡድን 20 አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ተካሄዷል። ጉባኤው በአፍሪካ የተካሄደው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመሪዎች ጉባኤ ላይ ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተሳተፉበት የቡድን 20 ጉባኤ እና የጎንዮሽ ውይይቶችን አስመልክቶ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በማብራሪያቸው ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ ጋባዥነት በጉባኤው ላይ መሳተፏን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጉባኤው ጎን ለጎን ከበርካታ ሀገራት መሪዎች እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጉባኤው አዘጋጅ ሀገር ደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ስሪል ራማፎሳ ጋር መወያየታቸውንና ውይይቱ በጉባኤው የአፍሪካን የጋራ ድምጽ እና ፍላጎት ማሰማትና ማንጸባረቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ እንደነበር አውስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከአቡዳቢ አልጋ ወራሽ ሼክ ካሌድ ቢን መሐሙድ ቢን ዛይድ አል ናህያን፣ ከፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታመር፣ ከኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዲክ ሾፍ እና ከሌሎች ሀገራት መሪዎች ጋር መምከራቸውን አመልክተዋል። ከእስያ ሀገራትም መካከል ከቪዬተናም፣ ኮሪያ ሪፐብሊክ እና ኢንዶኔዥያ መሪዎች ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። በባለብዙ ወገን መድረክም ከተባበሩት መንግስት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ ከአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ፣ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ እና ከዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ ጋር መምከራቸውንም እንዲሁ። በአፍሪካ ደረጃም ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሲድ ኡልድ ታህ ጋር መወያየታቸውን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በባለብዙ ወገን መድረክ እያደገ ያለውን ቁመና በማንሳት የበለጠ ትብብሮችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር መደረጉን ነው ፕሬስ ሴክሬተሪያቷ ያብራሩት። በሌላ በኩል በውይይቶቹ ኢትዮጵያ እያደረገች የምትገኘው የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ያስገኟቸው አመርቂ ውጤቶች እና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች እንዲሁም የኢኮኖሚ ማረጋጋት ተግባራት መነሳታቸውን ገልጸዋል። ሀገራትና ተቋማቱ ማሻሻያዎቹን እንዲደግፉም ጥሪ መቅረቡን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ እያደገ የመጣው ሚናዋ ሌላኛው የውይይቶቹ ትኩረት ነበር። ፕሬስ ሴክሬተሪያቷ ኢትዮጵያ በቅርቡ 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧን አውስተው፤ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድና ሁሉን አካታች እንዲሆን አጋሮች ድጋፍ በሚያደርጉበትና ኢትዮጵያ ልምድ በመቅሰም በምትችልበት ሁኔታ ላይ ውይይቶች መደረጋቸውን አመልክተዋል። ጉባኤው በሺዎች የሚቆጠሩ የሚሳተፉበት በመሆኑ ለቱሪዝም ልማት፣ ለመሰረተ ልማት ግንባታ እና ኢኮኖሚ እድገት ጉልህ አበርክቶ እንደሚኖረው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ላይ ንግግር ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎን በተካሄደው የኮምፓክት ፎር አፍሪካ ስብሰባ ላይ በመሳተፍ ባደረጉት ንግግር የበለጸጉ ሀገራት ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ፍላጎቶች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸውን አብራርተዋል። በአጠቃላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ውጤታማ እና ፍሬያማ ተሳትፎ ማድረጋቸውን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ የጉባኤው ተሳትፎ በዓለም የባለብዙወገን መድረኮች ላይ ያላት ቁመና የበለጠ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ኢትዮዽያ በሀገራዊ ሪፎርሙ ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው
Nov 24, 2025 141
አዲስ አበባ፤ ህዳር 15/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮዽያ በሀገራዊ ሪፎርሙ ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሀላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለፁ። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች ጋር ተወያይተዋል። አቶ አደም በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች ዘመናትን የተሻገረ ጠንካራ ግንኙነት አላቸው። ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ ትልቅ የልማት አጋር መሆኗን ጠቁመው የኢትዮጵያ የልማት እና የሪፎርም አጀንዳ እንዲሳካ ዩናይትድ ኪንግደም ለምትሰጠው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል። ሀገራቱ በየዘርፉ ያላቸው ጥልቅ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከር ብልፅግና ፓርቲ የሚጠበቅበትን ሚና እንደሚያጠናክርም አረጋግጠዋል። በትምህርት እና በጤና ዘርፍ ያላቸው አጋርነት ውጤታማ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ስኬታማ ትብብር በሌሎች ዘርፎችም ለማስፋት ቁርጠኛ ነን ብለዋል። በብልፅግና ፓርቲ አመራር ሰጪነት በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህን ስኬቶች ለማስቀጠል የሚደረገው ርብርብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ብልፅግና ፓርቲ ለተቋም ግንባታ ሥራዎች ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እና ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ ነጻ ገለልተኛ ተቋማት እውን መሆን ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል። የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ረገድም ፓርቲው ትልልቅ እርምጃዎችን መውሰዱን ገልጸው፤ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት በመንግሥት ካቢኔ እንዲካተቱ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል። ቀጣዩ ምርጫ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው፤ ምርጫው የህዝብ ተሳትፎ የተረጋገጠበት ተአማኒ እንዲሆን ብልፅግና ፓርቲ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር እና የአፍሪካ ኀብረት ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ዳረን ዌልች በበኩላቸው ኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ እና ምሳሌ የሚሆን ግንኙነት ያላቸው መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም በትክክለኛ መንገድ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በተሻለ ደረጃ እንደሚቀጥል አምናለሁ ብለዋል። ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ የተቋም ግንባታ ሥራዎችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን አምባሳደሩ አረጋግጠዋል።
ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር ትሰራለች 
Nov 24, 2025 125
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018(ኢዜአ)፦ ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ የፖለቲካ ቢሮ አባል እና የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ገለጹ። ኢትዮጵያ እና ቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩበት 55ኛ ዓመት ይከበራል። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ የሀገራቱን 55ኛ ዓመት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አስመልክቶ የደስታ መግለጫ መልዕክት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) አስተላልፈዋል። ዋንግ ዪ በመልዕክታቸው ቻይና እና ኢትዮጵያ ጥልቅ እና ለረጅም ጊዜ የቆየ ወዳጅነት እንዳላቸው ገልጸው ግንኙነታቸው በዓመታት መካከል ፀንቶ መቀጠሉን አመልክተዋል። ባለፉት 55 ዓመታት ሁለቱ ሀገራት የነበራቸው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በመልካም እምነት ላይ እና በአስፈላጊ ጊዜ እርስ በእርስ በመደጋገፍ ላይ የተመሰረተ መሆኑንም አመልክተዋል። ወዳጅነቱ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት አጋርነትና ትብብር ማሳያ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራቱ መሪዎች ስትራቴጂካዊ መሪነት የሁለትዮሽ ትብብሩ የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱንም ነው ያመለከቱት። ከምንጊዜውም በላይ የዳበረው የፖለቲካ የጋራ መተማመንና ፍሬያማ ተግባራዊ ትብብር መገለጫው የሆነው የሁለትዮሽ ግንኙነት ለሀገራቱ ህዝቦች ተጨባጭ ውጤቶችን ማስገኘቱን አብራርተዋል። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የ55ኛ ዓመቱን የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በዓል እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የቻይና አፍሪካ ትብብር ፎረም(ፎካክ) ጉባኤ ውጤቶችና የሀገራቱ መሪዎች የጋራ መግባባት ላይ የደረሱባቸውን ጉዳዮች ለመተግበር እንዲሁም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) የበለጠ ለማጠናከር ጥረት እንደሚያደርጉም አስታውቀዋል። በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የጋራ ራዕይን ማዕከል ያደረገ የቻይና-አፍሪካ ማህበረሰብ አዲስ የትብብር ምዕራፍ በመክፈቱ ላይ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1970 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ
የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ሎውረንስ ዎንግ ለይፋዊ ስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ
Nov 23, 2025 203
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 14/2018 (ኢዜአ)፦ የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ሎውረንስ ዎንግ ለይፋዊ ስራ ጉብኝት ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ለሚያደርጉት ይፋዊ ጉብኝት ዛሬ ማታ አዲስ አበባ ሲገቡ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቀባበል እንዳደረጉላቸው ገልጸዋል። ይህ ጉብኝት የሁለቱ ሀገራት አጋርነትን ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ ሲሆን፣ ተጨማሪ አዳዲስ የትብብር እድሎችን ለመዳሰስም ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ ከእ.አ.አ 2024 አንስቶ አራተኛው የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ። በተጨማሪም ዎንግ የሲንጋፖር የፋይናንስ ሚኒስትር ሲሆኑ ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 የሲንጋፖር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ሰርተዋል። ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1969 ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እ.አ.አ ጁን 2024 በሲንጋፖር ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ ከፕሬዝዳንት ታርማን ሻንሙጋራትናም እና ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ ጋር በሁለትዮሽ እና የባለብዙወገን ትብብር ዙሪያ ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ከሲንጋፖር ፕሬዝዳንት ጋር በኢስታና በፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ መለዋወጣቸውን ገልጸዋል። የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አማራጮችን ለመመልከት መስማማታቸውንም ተናግረዋል። የሀገራት መሪዎቹ የጉብኝት ልውውጥ በኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ያለውን ፍላጎት የሚያሳይ ነው። ሁለቱ ሀገራት በንግድና ኢንቨስትመንት፣ ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ቱሪዝም፣ ዘላቂ ልማት እና በሌሎች መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እየሰሩ ይገኛል።  
ማህበራዊ
አገልግሎቱ ለስደተኞችና ተመላሾች እየሰጠ ያለውን አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠል አለበት
Nov 24, 2025 29
አዲስ አበባ፤ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ለስደተኞችና ተመላሾች እየሰጠ ያለውን አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ። ቋሚ ኮሚቴው የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎትን የ2018 ዓ.ም የአንደኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።   የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ኃላፊ ጠይባ ሀሰን የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት፥ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከ34 ሀገራት የመጡ ከአንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን በ27 መጠለያዎች ውስጥ እንደምታስተናግድ ገልጸዋል። ተቋሙ የስደተኞችን አገልግሎት አሰጣጥ እና ደኅንነት ጥበቃ ሥራ ማጎልበት ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ባለፉት ሶስት ወራት እውቅና መስጠትና ምዝገባ፣ ዶክመንቴሽን፣ የደኅንነት ስጋትን መቀነስና ዘላቂ መፍትሄ ላይ አበረታች ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል። በተጨማሪም የጤና እና ትምህርት አገልግሎት ተደራሽነትን በማሳደግ፣ ለስደተኞች እና ተቀባይ ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ፈጠራና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን አስታውቀዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር)፤ አገልግሎቱ ለበርካታ ስደተኞች እየሰጠ ያለው አገልግሎት አበረታች መሆኑን ተናግረዋል።   በቀጣይም የሀገሪቱን ሠላምና ደኅንነት ባረጋገጠ መልኩ አገልግሎቱን ከሚመለከታቸው አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት አገልግሎቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አገልግሎቱ እየሰራ ያለውን ስራዎች አድንቀው፥ በቀጣይ በሀገሪቱ ላይ ጫናዎች እንዳይፈጠሩ ትኩረት አድርጎ መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። እንዲሁም በማህበራዊ አገልግሎት በሆኑ የጤናና ትምህርት አገልግሎቶች ላይ ጫናዎች እንዳይፈጠሩ ትኩረት ማድረግ ይገባል ነው ያሉት። ምክር ቤቱም አገልግሎቱ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የሥርዓተ- ጾታ እኩልነትና ፍትሃዊ የሃብት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ቅንጅታዊ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 24, 2025 64
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፡- የሥርዓተ- ጾታ እኩልነትና ፍትሃዊ የሃብት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ቅንጅታዊ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለፀ። የሥርዓተ- ጾታ ኦዲት መንግስት የሥርዓተ- ጾታ እኩልነትና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን ለማጠናከር የሚያግዝ ነው ተብሏል፡፡ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሴቶች ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጁትን ሥርዓተ- ጾታ ኦዲት ሰነድ የማስተዋወቅ መርሃ-ግብር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት አካሂዷል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር ወይዘሮ መሠረት ዳምጤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስት ተቋማት በሚያከናውኗቸው ተግባራት የሥርዓተ- ጾታ እኩልነት ጉዳይን አካትተው መሥራት ይጠበቅባቸዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የሥርዓተ- ጾታ እኩልነትን በተመለከተ በልዩ ሁኔታ መመልከት እንደሚገባ ተገንዝቦ የሥርዓተ -ጾታ ኦዲት ሰነድ ማዘጋጀቱን አስታውቀዋል። ይህም ሁሉን አቀፍ ኦዲት ለማካሄድ ያለውን የእውቀትና የክህሎት ክፍተትን በመቅረፍ ተቋማዊ አቅምን ከማጠናከር ባለፈ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አካታችነትን እንዲሁም የሥርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው ብለዋል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካይ አቶ አሳልፈው አመዲን የሴቶች፣ ህጻናት፣ አረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች ማህበራዊ ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችሉ ተግባራት እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር ስምምነት በመፈራረም የስርዓተ-ጾታ እኩልነትን የሚያረጋግጡ ተግባራት በጋራ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። በፌዴራል ዋና ኦዲተር እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሴቶች ኤጀንሲ ትብብር የተዘጋጀው የሥርዓተ- ጾታ ኦዲት ሰነድ የሥርዓተ- ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሴቶች ኤጀንሲ ምክትል ተጠሪ ሻራክ ዱሳቤ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ለሥርዓተ- ጾታ ኦዲት ትግበራ የሰጠችውን ትኩረት አድንቀዋል። የሥርዓተ- ጾታ ኦዲት ፍትሃዊ የሃብት አጠቃቀም ዙርያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመለየትና ለመፍታት የሚያስችል ነው ብለዋል። በፌዴራል ዋና ኦዲተርና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ትብብር የተዘጋጀው ሰነድ በጾታ እኩልነት፣ ተጠያቂነት እና መልካም አስተዳደር ዙሪያ ትብብርን እንደሚያጠናክር ገልጸዋል፡፡  
በጎንደር የቱሪዝም ልማቱና የከተማው ማስዋብ ስራዎች የጎብኚዎችን ቁጥር ለማሳደግ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል 
Nov 24, 2025 68
ጎንደር፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፡- በጎንደር እየተከናወነ ያለው የቱሪዝም ልማትና የከተማው ማስዋብ ስራዎች የውጭና የሀገር ውስጥ የጎብኚዎችን ቁጥር ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ ተገለጸ። የዘንድሮ የጎንደር የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ የሕዝቦችን አብሮነትና አንድነትን በሚያስተሳስስር መንገድ ከዋዜማው ጀምሮ በተለያዩ ሁነቶች ለማክበር ከወዲሁ ዝግጅት እየተደረገ ነው። የአማራ ክልል ባሕል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ዝግጅቱን በመገምገም ክትትልና ድጋፍ ማድረጉ ተመልክቷል። የቢሮው ሃላፊ አቶ መልካሙ ጸጋዬ በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ስራ የጎንደር ከተማን ዳግም ትንሳኤ ያበሰረ ታላቅ ታሪካዊ ክዋኔ ነው፡፡ ጥምቀትን ለማክበር የሚመጡ የውጭና የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች የታደሰውን ቤተ መንግስት እንዲጎበኙ በማድረግ የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራም ለበዓሉ ልዩ ድባብን የሚያጎናጽፍ መሆኑን ጠቁመው፤ የከተማው ሕዝብም እንግዶችን ተቀብሎ በማስተናገድ አይረሴ ቆይታ እንዲኖራቸው እንዲያደርግ የማመቻቸት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል። በጎንደር እየተከናወነ ያለው የቱሪዝም ልማትና የከተማው ማስዋብ ስራዎች የውጭና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎችን ቁጥር ለማሳደግና ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢም ለመጨመር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። በጎንደር ከተማ የጥምቀት በዓልን በስኬት ለማክበር እየተደረገ ያለውን ዝግጅት በመገምገም ቀሪ ተግባራትን በማመላከት ፈጥነው እንዲተገበሩ ለማስቻል በሥፍራው ተገኝተው ድጋፍ ማድረጋቸውን የቢሮው ሃላፊ አቶ መልካሙ ተናግረዋል፡፡ በክልሉ በርካታ የሰው ሰራሽ፣ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶችና ባሕላዊ እሴቶች ባለቤት መሆኑን ጠቅሰው፤ በወርሃ ጥር የሚከበረው የጥምቀት በዓልን ምክንያት በማድረግ እነዚህን ቅርሶች ለማስተዋወቅ አጋዥ ሚና እንደሚጫወት አስረድተዋል። በክልሉ ነባርና አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን በማልማት፣ በመጠበቅና በመንከባከብ መንግስት እያከናወነው ያለው ተግባር ለቱሪዝም ዘርፉ መነቃቀት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባሕልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ማሪያሟ ካሳሁን በበኩላቸው፤ የጥምቀት በዓልን በስኬት ለማክበር በዐቢይ ኮሚቴ የሚመራ ስምንት ንዑሳን ኮሚቴዎችን በማዋቀር ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል። በዓሉን ምክንያት በማድረግ አብሮነት፣ ወንድማማችነትና አንድነትን የሚያስተሳስርና የሚያጠናክር የባሕል ፌስቲቫል ከበዓሉ አንድ ሳምንት ቀድሞ እንደሚዘጋጅ አስረድተዋል። በፌስቲቫሉ ላይም ባሕላዊ እሴትና ትውፊቶችን የሚያንጸባርቁ የጎዳና ላይ ትዕይንቶች እንደሚቀርቡ ጠቁመው፤ ይህም የቱሪስቶችን ቆይታ በማራዘም የከተማውን ሕዝብ ከቱሪዝም ዘርፉ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል።  
በአፋር ክልል አርብቶ አደር አካባቢዎች የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Nov 24, 2025 125
ሠመራ፣ ህዳር 15/2018(ኢዜአ)፡- በአፋር ክልል አርብቶ አደር አካባቢዎች የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋት እየተደረገ ያለው የተቀናጀ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ። በክልሉ ወሰማ ወረዳ የተገነባው አዲስ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዛሬ ተመርቋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት አስተዳደር ቢሮ ኀላፊ አቶ ኡመር ኑሩ፤ ከሃገራዊ ለውጡ ወዲህ የክልሉ መንግሥት፣ ሕብረተሰቡን፣ ባለሀብቶችንና ሌሎችንም አጋር አካላት በማስተባበር የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋት ጥረት ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰዋል። ይህም ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። በወሰማ ወረዳ የተገነባው ትምህርት ቤት ላለፉት ዓመታት ሕብረሰተቡ ሲያናሳው ለቆየው ጥያቄ ምላሽ የሰጠ መሆኑንም አንስተዋል። በቀጣይነትም ለትምህርት ቤቱ የሚያስፈልጉትን ግብአቶች በማሟላት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲሰጥ የክልሉ መንግስት ተከታትሎ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሳ አደም በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ትምህርትን በፍትሃዊነት ማዳረስ የክልሉ መንግስት ዋነኛ ትኩረት ነው። ለምረቃ የበቃው ትምህርት ቤት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ለመከታተል አብአላና በራህሌ ድረስ ረጅም ርቀት ይሄዱ የነበረውን ያስቀረ መሆኑንም ገልፀዋል። ትምህርት ቤቱ የተገነባው የትምህርት ቢሮና ኢዱካንሰ ፋውንዴሽን ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በ14 ሚሊዮን ብር ወጪ መሆኑን አስታውቀዋል። የድርጅቱ ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ለሜሳ፤ መንገስት የትምህረት ተደራሽነትን ለማስፋት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ በመደገፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የክልልና የዞን አመራሮች፣ የወረዳ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።  
ኢኮኖሚ
መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የብዝሃ-ዘርፍ የኢኮኖሚ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን መደላድል ፈጥሯል
Nov 24, 2025 35
ድሬደዋ፣ ህዳር 15/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ የብዝሃ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ጉዞ እንዲሳካ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ተናገሩ። ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ዛሬ ድሬ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የስራ እንቅስቃሴን ተመልክተዋል። ኮሚሽነሩ በወቅቱ እንዳሉት፤ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ የዘመናት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እየፈታ ይገኛል። ከወረቀትና ከሰው ንክኪ የፀዱ አገልግሎቶች ተደራሽ መደረጋቸው ደግሞ ብልሹ አሠራሮችንና የሙስና ተግባራትን እንደሚቀንሱ ገልጸዋል። ይበልጡኑ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎቶች ተደራሽ መሆናቸው እንደ አገር ለተጀመሩ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ ግስጋሴዎች ዳር መድረስ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል። በድሬደዋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዚሁ ጅምር ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፥ የተጀመረውን ስራ ለማሳደግ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ፥ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በስፋትና በጥራት በመላው አገሪቷ ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል። የድሬደዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሐይር ሐጂ ኑር በበኩላቸው፥ በድሬ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት 10 ተቋማት 28 አገልግሎቶችን በጥራትና በፍጥነት ለተገልጋዮች ተደራሽ እያደረጉ መሆኑን አንስተዋል። ባለፉት ሁለት ወራት ከአራት ሺህ በላይ ለሚሆኑ ነዋሪዎች የተቀናጀ አገልግሎት መሰጠቱን ጠቅሰው፥ የተጀመረውን ስራ ለማስፋትና ለማሳደግ ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል። የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ዛሬ ረፋድ ላይ በድሬዳዋ ከተማ የተገነባውን የመጀመሪያ ምዕራፍ የኮሪደር ልማትንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በመዲናዋ ለአምራቾች በተሰጠው ትኩረት በምርታማነትና በገበያ ማረጋጋት ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል
Nov 24, 2025 31
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018(ኢዜአ)፡- በመዲናዋ አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርታማነትን በማሳደግ የገበያ ማረጋጋት ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ በተሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ለውጦች መገኘታቸውን የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር ገለጹ። 20ኛውን የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የተዘጋጀው ከተማ አቀፍ ኤግዚቢሺንና ባዛር ተከፍቷል። ለተከታታይ ሦስት ቀናት በሚቆየው በዚሁ ኤግዚቢሽንና ባዛር ገበያን የሚያረጋጉ የተለያዩ ምርቶች ቀርበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የለውጡ መንግሥት ህብረ-ብሄራዊ ፌደራሊዝምን የማጠናከርና ቀድሞ የነበሩ ጉድለቶችን የማረም ስራ ሰርቷል። ይህም ዜጎች ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር አካባቢያቸውን ይበልጥ እንዲያለሙ ትልቅ እድል ፈጥሯል ብለዋል። በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛር ኢንዱስትሪዎች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ ተሞክሮና ልምድ እንዲለዋወጡ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል። በራስ ምርት የመጠቀምና የመኩራት ባህል እንዲጎለብት እንዲሁም የኢትዮጵያን እንግዛ ንቅናቄን የበለጠ ውጤታማ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል። በኤግዚቢሽንና ባዛሩ የቀረቡ ምርቶች የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ትግበራ ፍሬ እያፈራ እንደሚገኝ የሚያመላክቱ፣ ገበያን የሚያረጋጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በመዲናዋ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት በተጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰው፥ ኢንዱስትሪዎቹ ለበርካቶች የስራ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል። ከተማ አስተዳደሩ የምርትና አገልግሎት ማሳያ፣መሸጫና የገበያ ትስስር መፍጠሪያ መድረኮችን በማስፋት ለኢንዱስትሪዎች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ፀጋዬ ደበሌ በበኩላቸው፥ በኤግዚቢሽንና ባዛሩ 130 የሚሆኑ አምራቾች ምርታቸውን የሚያቀርቡ መሆኑን ገልጸዋል። ኢንዱስትሪዎች፣ በከተማ ግብርና የተሰማሩ አምራቾችና ሸማች ህብረት ስራ ማህበራት የተሳተፉበት ኤግዚቢሽንና ባዛሩ ሸማቾችና አምራቾችን ቀጥታ በማገናኘት የዋጋ ንረትን መከላከልን ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። በኤግዚቢሽንና ባዛሩ የተሳተፉ አምራቾች በሰጡት አስተያየት፥ የተለያዩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረባቸውን ተናግረዋል። ከኤግዚቢሽንና ባዛሩ በተጓዳኝ የደም ልገሳ መርሃ ግብርም ተካሂዷል።
አፍሪካ በአውሮፓ ገበያ ያላትን ተደራሽነት ለማሳደግ ታሪፍ እና ታሪፍ ያልሆኑ ገደቦች ሊነሱ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Nov 24, 2025 39
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 15/2018 (ኢዜአ)፡- አፍሪካ በአውሮፓ ገበያ ውስጥ ያላት ድርሻ እና ተደራሽነት እንዲጨምር ታሪፍና ታሪፍ ያልሆኑ ገደቦች መነሳት እንደሚገባቸው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሰባተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ በአንጎላ ሉዋንዳ ተጀምሯል። ጉባኤውን የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾና የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት አንቶኒዮ ኮስታ በጋራ መርተውታል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ የህብረቱ ሀገራት መሪዎች፣ የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን እና ሌሎች የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ ወጣቶች፣ የሲቪክ ማህበራት እና የንግድ ልዑካን በጉባኤው ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ። ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር አፍሪካ በቅርቡ የዓለም እድገት ኃይል ምንጭ እንደምትሆን ገልጸዋል። የተትረፈረፈ የገበያ እድል፣ የሰው ኃይል እና የተፈጥሮ ሀብቶች የዓለም እድገት ዋንኛ ተዋናይ የሚያደርጓት አቅሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ሊቀ መንበሩ በአፍሪካ እና በአውሮፓ መካከል ሚዛናዊ የሆነ የንግድ አጋርነት ሊኖር እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በአፍሪካ ያለው የአውሮፓ ኢንቨስትመንት መጨመር እንዳለበትም አንስተዋል። አፍሪካ ሀገራት ወደ አውሮፓ ህብረት ገበያ በሚፈለገው መጠን እንዳይገቡ ያደረጋቸው የታሪፍ እና ከታሪፍ ጋር ያልተያያዙ ገደቦች እንዲነሱም ጠይቀዋል። እኩልነት እና የጋራ ፍላጎቶችን መሰረት ባደረገ መልኩ ጠንካራ የባለብዙወገን ትብብር መገንባት እንደሚገባ አሳስበዋል። ሰላም፣ ደህንነት፣ የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት፣ ፍልሰት እና የሰዎች እንቅስቃሴና የሰው ኃይል ልማት መሪዎቹ ውይይት ከሚያደርጉባቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የተቋማቱ መሪዎች ለባለብዙ ወገን ትብብር፣ አጋርነት እና እየታዩ ላሉ ፈተናዎች የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የሚወያዩባቸው ጉዳዮች በአጀንዳ 2063፣ በዘላቂ የልማት ግቦች እና የአፍሪካ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት የ2030 የጋራ ራዕይ ጋር የተቆራኙ መሆናቸውም ተመላክቷል። ከዋናው የመሪዎች ጉባኤ አስቀድሞ የወጣቶች እና የሲቪክ እንዲሁም የንግድ ፎረሞች መካሄዳቸው ይታወቃል። ሰባተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እስገ ነገ ይቆያል።
የቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ ስራዎች ለዓለም ለማሳወቅ መልካም አጋጣሚን ፈጥሯል- ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)  
Nov 24, 2025 83
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ላይ መሳተፏ እያከናወነቻቸው ያሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ለዓለም ማህበረሰብ ለማሳወቅ ምቹ ሁኔታን እንደፈጠረላት የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የቡድን 20 አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ለመጀመሪያ ጊዜ ተካሄዷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመሪዎች ጉባኤ ላይ ተሳትፈዋል። ይህን አስመልክቶ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ በቡድን 20 ላይ የተጋበዘቸው መታየት ያለባቸው መስፈርቶችን ስላሟላች ነው፤ ከተጋበዙ ሀገራትም ቅድሚያ ከሚሰጣቸው መካከል ናት ብለዋል። በዚህም መሠረት በኢኮኖሚ መጠን፣ ለቀጣናው ብሎም ለአፍሪካ ባላት ሚና እንዲሁም አሁን እየተከናወኑ ያሉ የለውጥ ሥራዎችን መሠረት በማድረግ በስብሰባው ላይ መጋበዟን ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ መድረኩ የአፍሪካ ሀገራት ድምጽ እንዲሰማበት ማድረግ የሚያስችል ሐሳብ ማንሳታቸውንም አመላክተዋል። የዓለም አሥተዳደር፣ የኢኮኖሚ ብሎም ፋይናንስ አሥተዳደር እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከተ ምን መሆን አለበት በሚለው ላይም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ነው ያነሱት። መድረኩ ኢትዮጵያ እየሠራች ያለውን ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ለመግለጽ ጥሩ አጋጣሚ መሆኑንም ጠቁመዋል ሚኒስትሯ። የኢትዮጵያ ድምጽ ትልቅ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ በቡድን 20 የመሪዎች ስብሰባ በተጋባዥነት መሳተፏ የኢትዮጵያን መታየት በደንብ አድርጎ መጨመሩን ተናግረዋል። አክለውም ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያሳየች ያለው ዕድገት፣ ካላት የቆዳ ስፋት፣ የሕዝብ ብዛት በአጠቃላይ ካለችበት ለውጥ አንጻር ዝም ልትባል አትችልም ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በመድረኩ ብዝኀ ወገን የሚለው ሐሳብ አዋጭ መሆኑን አንስተዋል፤ አፍሪካን በየትኛውም ዘርፍ ያላካተተ አካሄድ የትም እንደማይደርስም ተስተጋብቷል ብለዋል። ከስብሰባው ጎን ለጎንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከበርካታ ሀገራት መሪዎች ጋር መምከራቸውን ገልጸው፤ ውይይቶቹ የሚያሳዩት የኢትዮጵያ ተፈላጊነት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ነው ሲሉ በአጽንኦት ገልጸዋል። መሪዎቹም የኢትዮጵያን ልማት እንዲደግፉ፣ በኢንቨስትመንትና በንግድ ዙሪያ ውይይቶች መደረጋቸውን አመላክተዋል። በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ ትልቅ ትርጉም ያለው ስብሰባ ነበር ያሉት ሚኒስትሯ፤ የቡድን 20 ሀገራት ስብሰባ በአፍሪካ ምድር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑንም አንስተዋል።  
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምር ስራዎች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል
Nov 24, 2025 231
አምቦ፤ ሕዳር 15/2018(ኢዜአ)፦ የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የጥናትና ምርምር ስራዎች ላይ ማተኮር እንዳለባቸው የጤና ዘርፍ መምህራን አመለከቱ። የጤና ትምህርት አሰጣጥን በማዘመን ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያ ማፍራት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተካሄዷል።   በመድረኩ ላይ የተሳተፉት የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ረዳት ፕሮፌሰር ሙሉ ኪታባ፣ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሀይል ማፍራት አስፈላጊ ነው ብለዋል። ለተግባራዊነቱም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የሰው ሀይል ለማፍራት በተግባር የተደገፈ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ማካሄድ እንዳለባቸው አስረድተዋል።   የጤና ትምህርት አሰጣጥን ማዘመን መንግስት ተግባራዊ ያደረገውን የበሽታ መከላከልና አክሞ የማዳን የጤና ስራ ለማሳካትም መሰረት መሆኑን ተናግረዋል። በአምቦ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት የተካሄደው የምክክር መድረክም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰው የአምቦ ዩኒቨርሲቲም የጤና ትምህርት አሰጣጥን በጥናትና ምርምር በማስደገፍ ከዘመኑ ጋር ማጣጣም ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል። በተለይም አምቦ፣ ጅማ እና የኖርዌይ ቪ.አይ.ዲ ዩኒቨርሲቲ በጋራ የጤና ዘርፍ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የሚያደርጉትን የጥናትና ምርምር ስራዎች የህብረተሰቡን ችግር በተጨባጭ እንዲፈቱ የማማከር ስራዎችን በጋራ ያከናውናሉ ብለዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ረዳት ፕሮፌሰር አበበ አበራ በበኩላቸው፤ የጤና ትምህርትን ውጤታማ ለማድረግ የምሁራን እና ባለድርሻ አካላት ትብብር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።   በአምቦ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት የተካሄደው የምክክር መድረክም የጤና ትምህርት አሰጣጡን በተግባር በማስደገፍና የጥናት እና ምርምር ስራዎች የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱ የፖሊሲ ሀሳቦች እንዲሆኑ የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰዋል።   የኖርዌይ ቪ.አይ.ዲ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ተስፋዬ ለታ (ዶ/ር)፤ የጤና ትምህርት አሰጣጥን ወቅቱ በደረሰበት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ መሰጠቱ ብቁና ተወዳዳሪ የጤና ባለሙያ ለማፍራት እንደሚያግዝ ገልጸዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲዎቹ የጀመሩት ትብብር ዘርፉን ለማሻሻል በጎ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
ታዳሽ ኃይል መጠቀም የሚያስችል የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሥርዓት በመዘርጋት ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል
Nov 23, 2025 175
አዲስ አበባ፤ ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል መጠቀም የሚያስችል የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሥርዓት በመዘርጋት ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስቴሩ ከፓወር አፍሪካ ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀው ሁለተኛው ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኤግዚቢሽንና ባዛር ከታኅሣሥ 9 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ያካሂዳል፡፡   ሚኒስትሩ አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ሁለተኛውን ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኤግዚቢሽንና ባዛር ለማካሄድ በተደረጉ ዝግጅቶችና በሚጠበቁ ውጤቶች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት መተግበር የጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ መደላድል እየፈጠረ ነው። የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ሥራዎች ኢትዮጵያ የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ(COP32) እንድታስተናግድ እንድትመረጥ አድርጓታል ሲሉም ገልጸዋል። በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ታዳሽ ኃይልም ሆነ ዝቅተኛ በካይ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።   ከታኅሣሥ 9 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚካሄደው ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ ኤግዚብሽንና ባዛር ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል። በኤግዚቢሽን እና ባዛሩ ላይ ኤሌክትሪክን ጨምሮ የተለያዩ ታዳሽ ኃይል የሚጠቀሙ ተሽከርካሪ አምራቾች፣ ቴክኖሎጂ አቅራቢዎች፣ በዘርፉ የተሰማሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የጥናትና ምርምር ተቋማት እንደሚሳተፉ አብራርተዋል። በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችና መፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ በጋራ ውይይት የሚደረግበት መርሐ ግብር መሰናዳቱንም ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉዳያችንን በአጭር ግዜ መጨረስ አስችሎናል - ተገልጋዮች
Nov 23, 2025 108
ሀዋሳ፤ ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ መጨረስ እንዳስቻላቸው በሀዋሳ ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገለጹ። በሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የ12 ተቋማት 38 አገልግሎቶች እየተሰጠ መሆኑን የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አስታውቀዋል። የሲዳማ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ከጀመረበት መስከረም አጋማሽ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለ1ሺህ 300 ሰዎች አገልግሎት መስጠቱ ተገልጿል። በማዕከሉ የሲዳማ ክልል ንግድ ቢሮ፣ ገቢዎች ባለስልጣን፣ ጤና ቢሮ እና የሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን ጨምሮ የ12 ተቋማት አገልግሎቶች በማዕከሉ ይሰጣሉ። እነዚህ ተቋማት በአንድ ማዕከል ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠታቸው እንግልት፣ አላስፈላጊ ወጪና ጊዜ በመቆጠብ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸውም ተገልጋዮች ገልጸዋል። ኢዜአ በማዕከሉ ጉዳያቸውን ሲያስፈጽሙ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች እንደገለጹት ቀደም ሲል በተበታተነ ስፍራ ሲሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ውስጥ ማግኘታቸው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ መጨረስ አስችሏቸዋል።   በማዕከሉ አገልግሎት ለማግኘት የመጡት ወይዘሮ የሺመቤት ተረፈ እንዳሉት ቀደም ሲል በተለያዩ ቦታዎች ሲሰጡ የነበሩ የመንግስት አገልግሎቶችን በአንድ ስፍራ እያገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል። የማዕከሉ አገልግሎት ረጅም ውረፋ ከማስቀረት ባለፈ የተገልጋይን እንግልትና የሚባክን ጊዜ ማስቀረቱን ገልጸዋል።   ውክልና ለመስጠት ወደ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ እንደመጡ የገለጹት ሌላው አስተያየት ሰጪ ሄኖክ አደራ በበኩላቸው በማዕከሉ ፈጣን አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ከበር ጀምሮ ጥሩ መስተንግዶ ማግኘታቸውን ጠቁመው፣ ማዕከሉ ከቀበሌ ጀምሮ ወደ ተለያዩ ተቋማት ሲመላለሱ ሲገጥማቸው የነበረን እንግልት የበዛበት አሰራርን ማስቀረቱንና ባገኙት አገልግሎት መደሰታቸውን ገልጸዋል።   በማዕከሉ አገልግሎት እየሰጡ ካሉ ተቋማት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ባለሙያ እንዳሻው ኤራንጎ ቀደም ሲል ደንበኞች ቲን ቁጥር ለማግኘት ወደ ባለስልጣኑ ሲመጡ አሻራ ሰጥተው የፋይዳ መታወቂያ እንዲያወጡ ኢትዮ ቴሌኮም እንልካቸው ነበር ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ግን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ አገልግሎቶች ስለሚሰጡ ተገልጋዩ ሁሉንም አገልግሎቶች በማዕከሉ እያገኘ በመሆኑ ተጠቃሚ መሆኑን ገልጸዋል።   የሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እንግዳየሁ ዘውዴ እንዳሉት በማዕከሉ 12 የፌዴራል፣ የሲዳማ ክልልና የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ተቋማት 38 አገልግሎቶችን ይሰጣሉ። ማዕከሉ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ወዲህ እስካሁን ድረስ ለ1ሺህ 300 ተገልጋዮች አገልግሎት መስጠቱን ጠቅሰው፣ ተገልጋዩ ባገኘው አገልግሎት ላይ በሰጠው አስተያየትና እርካታ እያገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
ባለስልጣኑ ዲጂታል አሰራሮችን በመዘርጋት ተገልጋዩ ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ አድርጓል
Nov 23, 2025 110
ድሬዳዋ፣ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ዲጂታል አሰራሮችን በመዘርጋት ህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ የትራስፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ እየተጋ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን ገለፀ። በባለስልጣኑ የመንገድ ትራፊክ ደህንነትና የመድን ፈንድ ዳይሬክተር ኢንጂነር ሁሴን ጀማል ለኢዜአ እንደገለፁት፥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የትራንስፖርት ዘርፍ አገልግሎቶችን ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ ናቸው። በተለይም አዲሱ የድሬዳዋ መናኸሪያ ተርሚናል በዘመናዊ መንገድ መገንባቱና ዲጂታል አገልግሎቶች ተደራሽ መደረጋቸው ቀደም ሲል የነበሩ ትርምሶችና መጨናነቆችን አስቀርቷል ብለዋል። የጉዞ ትኬት በኢ-ቲኬቲንግ አሰራር መቀየሩ፣የትራፊክ ደንብ የሚተላለፉ ቅጣታቸውን በቴሌብር እንዲከፍሉ መደረጉ ከዚህ በፊት ይባክን የነበረን የስራ ጊዜና ጉልበት ማስቀረት አስችሏል ብለዋል። በተለይም ተጓዦች በተደጋጋሚ ጊዜ ሲያቀርቡ ለነበሩት የተጋነነ የትራንስፖርት ክፍያን በመከላከል ፍትሃዊ እና ተደራሽ አገልግሎቶች እንዲያገኙ ማስቻሉን ገልጸዋል። እንደ ኢንጂነር ሁሴን ገለፃ፥ ባለስልጣኑ የጀመራቸውን የዲጂታል አገልግሎቶች በማሳደግ ስማርት ድሬዳዋን የሚመጥን አገልግሎቶች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል። የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ዘውገ አውላቸው በበኩላቸው፥ የዲጂታል አገልግሎቶቹ ከድሬዳዋ ወደ ተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች በሚወጡና በሚገቡ የህዝብ ትራንስፖርቶች እና በከተማዋ ታክሲዎች ላይ ተደራሽ መደረጉን ገልጸዋል። አሽከርካሪዎች ጉዳያቸውን ካሉበት ስፍራ ሆነው በዲጂታል አገልግሎቱ እየተጠቀሙ ይገኛሉ ብለዋል። በተጨማሪም የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች የትምህርት አሰጣጥን በዲጂታል ካሜራ በመከታተል ብቃትና ስነምግባር የተላበሱ ባለሙያዎችን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከድሬዳዋ-ሐረር ህዝብ የሚያመላልሰው የሚኒባስ አሽከርካሪ አቶ ሰይፈዲን አልይ እና የታክሲ አሽከርካሪው አቶ ጋሻው ሀብታሙ እንዳሉት፥ ባለስልጣኑ የጀመራቸውን የዲጂታል አገልግሎቶች ጊዜንና ጉልበትን ለስራ በማዋል ውጤታማ ስራ ለመስራት አስችሏቸዋል። አንድን ጉዳይ ለማስፈፀም ከግማሽ ቀን በላይ ማባከን ቀርቷል ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ፤ ይኸም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባ ብለዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ በብስክሌት ስፖርት እያስመዘገበች ያለው ውጤት እንዲያድግ የበለጠ መስራት ይገባል- የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር
Nov 24, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በዓለም እና አህጉራዊ የውድድር መድረኮች ላይ በብስክሌት ስፖርት እያስመዘገበች ያለው ውጤት እንዲጠናከር አበክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፀጋዬ ማሞ ገለጹ። በኬንያ ክዋሌ ከተማ በተካሄደው 19ኛው የአፍሪካ ብስክሌት ሻምፒዮና ላይ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ዛሬ አዲስ አበባ ገብቷል። ልዑካን ቡድኑ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፀጋዬ ማሞ እና የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገውለታል። ሚኒስትር ዴኤታ ፀጋዬ ማሞ መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ምቹ ዕድል እንደ ሀገር አሸናፊ ቡድን ለመገንባት ማስቻሉን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ ብስክሌት ስፖርት ልክ እንደ አትሌትክሱ ሁሉ የአረንጎዴ ጎርፍ ታሪክን እየደገመ ነው ሲሉ ገልጸው ውጤት ለማሳደግ የበለጠ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል። መንግስት ለብስክሌት ስፖርት የሚያደርግውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት እና የአፍሪካ ብስክሌት ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አቶ ወንድሙ ኃይሌ ኢትዮጵያ በብስክሌት ስፖርት የምትኮራባቸው ስፖርተኞች ተፈጥረዋል ሲሉ ተናግረዋል። በኬንያ የተካሄደው ሻምፒዮና የአፍሪካዊያን ዓይን ወደ ኢትዮጵያ ያዞረና ባንዲራችን እንዲውለበለብ ያደረገ ነው ብለዋል። ውድድሩ ለብስክሌተኞቹ በቀጣይ በዓለም የብስክሌት ሻምፒዮና ላይ እንዲሳተፉ እድል የፈጠረ መሆኑን አመልክተዋል። በ19ኛው የአፍሪካ ብስክሌት ሻምፒዮና ከ29 ሀገራት የተሳተፉ ብስክሌቶች የተወዳደሩ ሲሆን ኢትዮጵያም በሁለቱም ጾታዎች 10 ብስክሌተኞች አሳትፋለች። በዚህም ውድድር ላይ ተወዳዳሪዎቹ በአዋቂ፣ ታዳጊ ወጣቶች እና ከ23 አመት በታች ተሳትፈዋል። በዚህም በብስክሌተኛ ፅጌ ካህሳይ በግል ሰዓት ሙከራ ውድድርና በጎዳና ላይ ውድድር ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ ኢትዮጵያ አግኝታለች። በጎዳና ውድድር ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ ቅሳነት ግርማይ 3ኛ ደረጃ ይዛ ነሐስ ሜዳሊያ በማግኘት ስታጠናቅቅ ራሄል ታመነ 4ኛ በመውጣት በአጠቃላይ ውጤት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋን የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ በሴካፋ ዞን ማጣሪያ ለግማሽ ፍጻሜ አለፈች
Nov 24, 2025 66
አዲስ አበባ፤ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦ አዘጋጇ ኢትዮጵያ በ16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ለግማሽ ፍጻሜ ማለፏን አረጋገጠች። በምድብ አንድ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል። ሶማሊያ ሩዋንዳን 3 ለ 0፣ ኬንያ ደቡብ ሱዳንን 2 ለ 0 አሸንፈዋል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኬንያ በሰባት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ሶማሊያ በምድቧ ያደረገችውን አራት ጨዋታዎች አጠናቃ በስድስት ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። ደቡብ ሱዳን በአንድ አራተኛ እና ሩዋንዳ ያለ ምንም ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዘዋል። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በሰባት ነጥብ ተመሳሳይ ነጥብ ያላትን ኬንያን በግብ ክፍያ በልጣ አንድ ጨዋታ እየቀራት ለግማሽ ፍጻሜ አልፋለች። ኬንያም ለግማሽ ፍጻሜው ማለፏን አረጋግጣለች። ኢትዮጵያ ለግማሽ ፍጻሜ ያለፈችው ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳንና ሩዋንዳ በነጥብ የማይደርሱባት በመሆኑ ነው። አዘጋጇ ኢትዮጵያ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋን ከነገ በስቲያ ከኬንያ ጋር ታደርጋለች። ኢትዮጵያ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋን ከነገ በስቲያ ከኬንያ ጋር ታደርጋለች። በምድብ ሁለት ታንዛንያ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፏ ይታወቃል።  
ኬንያ ደቡብ ሱዳንን አሸነፈች 
Nov 24, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፦ በ16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካ ዞን ማጣሪያ ኬንያ ደቡብ ሱዳንን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተደረገው የምድብ አንድ ጨዋታ ዴሪክ ዋንዮንዪ በ12ኛው እና ትሬቨር ናሳሲሮ በ89ኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ድሉን ተከትሎ ኬንያ በሰባት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። በውድድሩ ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ደቡብ ሱዳን በአንድ ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። በዚሁ ምድብ ዛሬ በተካሄደ ጨዋታ ሶማሊያ ሩዋንዳን 3 ለ 0 አሸንፋለች። የማጣሪያው አዘጋጅ ሀገር ኢትዮጵያ ምድቡን በሰባት ነጥብ እየመራች ትገኛለች። በተያያዘም በምድብ ሁለት በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ታንዛንያ ብሩንዲን 5 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች። ሳዳም ሁሴኒ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሲሰራ እድሪሳ ካይለንዴሞ እና ኢስማኤል ላይኩንጊሎ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ታንዛንያ በ12 ነጥብ የምድብ መሪነቷን አጠናክራለች። በብሄራዊ ቡድን ለግማሽ ፍጻሜው ያለፈ የመጀመሪያ ቡድን መሆኑ ይታወቃል። በዚሁ ምድብ ጅቡቲ ከሱዳን ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
ዝቅተኛ በካይ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል ርብርብ እየተደረገ ነው
Nov 24, 2025 122
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፡- በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ዝቅተኛ በካይ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስቴሩ ከፓወር አፍሪካ ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀው ሁለተኛው ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኤግዚቢሽንና ባዛር ከታኅሣሥ 9 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ያካሂዳል፡፡ ሚኒስትሩ አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ሁለተኛውን ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኤግዚቢሽንና ባዛር ለማካሄድ በተደረጉ ዝግጅቶችና በሚጠበቁ ውጤቶች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።   ሚኒስትር አለሙ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት መተግበር የጀመረው አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ መደላድል እየፈጠረ ነው። የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ሥራዎች ኢትዮጵያ ኮፕ 32 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እንድታስተናግድ እንድትመረጥ አድርጓታል ሲሉም ጠቅሰዋል። በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍም ታዳሽ ኃይልም ሆነ ዝቅተኛ በካይ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ከታኅሣሥ 9 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚካሄደው ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ ኤግዚብሽንና ባዛር ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል።   በኤግዚቢሽን እና ባዛሩ ላይ ኤሌክትሪክን ጨምሮ የተለያዩ ታዳሽ ኃይል የሚጠቀሙ ተሽከርካሪ አምራቾች፣ ቴክኖሎጂ አቅራቢዎች፣ በዘርፉ የተሰማሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የጥናትና ምርምር ተቋማት እንደሚሳተፉ አብራርተዋል። በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችና መፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ በጋራ ውይይት የሚደረግበት መርሐ ግብር መሰናዳቱንም አመልክተዋል።
በገጠር ክላስተሮች እየተከናወነ ያለው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ምርታማነትን ለማሳደግ እያገዘ ነው
Nov 22, 2025 173
ድሬዳዋ፤ ሕዳር 13/2018(ኢዜአ) ፡- በድሬዳዋ የገጠር ክላስተሮች እየተከናወነ ያለው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለስነ ምህዳር ጥበቃና ምርታማነትን ለማሳደግ እያገዘ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ገለጸ። በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ባለሙያ አቶ ገረመው ረጋሳ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በድሬዳዋ የገጠር ክላስተሮች የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራ በስፋት በመከናወን ላይ መሆኑንና በዚህም ውጤት እየመጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   በድሬዳዋ የገጠር ክላስተሮች እየተከናወነ ያለው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለስነ ምህዳር ጥበቃና ምርታማነትን ለማሳደግ እያገዘ ስለመሆኑ አንስተዋል። በዘመቻ እና በመደበኛ መርሃ ግብር በተራቆቱ ተፋሰሶች ላይ በተከናወኑ የልማት ስራዎች ከ60 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ማልማት መቻሉን ተናግረዋል። በዚህም የአካባቢን ስነ ምህዳር ከመጠበቅም ባለፈ ምርታማነትን ማሳደግ ማስቻሉን ገልጸዋል። በቢሮው የህብረት ስራ ማስፋፊያ፣ ግብይትና ግብአት ኤጀንሲ ባለሙያ አቶ ያሲን ኢብራሂም፤ የተፋሰስ ልማት ስራ የአካባቢ ስነ ምህዳርን በመጠበቅ ረገድ የሚታይ ውጤት የመጣበት መሆኑን ተናግረዋል።   በተለይም በገጠር አካባቢዎች ምርታማነትን በማሳደግ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያስቻለ መሆኑንም አንስተዋል። በድሬዳዋ የገጠር ክላስተሮች ወጣቶችና ሴቶች ተደራጅተው በሌማት ትሩፋት ኢንሸቲቮች ላይ በመሳተፍ ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል። የለገ ዶል ገጠር ቀበሌ አርሶ አደር ኢብሳ ሙሳ እና አርሶ አደር አህመድ ዳዌ፤ በአካባቢው የተከናወነው የልማት ስራ በብዙ መልኩ የጠቀማቸውና ውጤትም ያገኙበት መሆኑን ተናግረዋል።   የቀበሌው የግብርና ባለሙያ አቶ ምህረት መታዬት፤ አርሶ አደሮቹ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በእንስሳት እርባታ በመሰማራት ስኬታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።  
ኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤን እንድታስተናግድ መመረጧ ሀገሪቷ ለአየር ንብረት ለውጥ ፖሊሲና ስትራቴጂ ትግበራ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠ ነው 
Nov 21, 2025 236
አዲስ አበባ፤ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት (COP-32) ጉባኤን እንድታስተናግድ መመረጧ ሀገሪቷ ለአየር ንብረት ለውጥ ፖሊሲና ስትራቴጂ ትግበራ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠ ነው ሲሉ የአረንጓዴ አሻራ ሀገራዊ መርሃ-ግብር የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) ገለፁ። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬቶችም ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝም ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአካባቢ ስነ-ምኅዳር ደኅንነት በማስጠበቅ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። ኢትዮጵያ በብራዚል ቤለም በተካሄደው የዓለም የአየር ንብረት (COP-30) ጉባኤ ላይ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት (COP-32) ጉባኤ ለማስተናገድ መመረጧ ይታወቃል። አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉትም፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ዓለም አቀፍ ዕውቅናን ያስገኘ አስደማሚ የልማት ስኬት ተመዝግቧል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬትም 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP-32) ለማስተናገድ ተመራጭ እንድትሆን ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ገልጸዋል። ጉባኤው ላይ የበርካታ ሀገራት መሪዎች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች ምክክር በማድረግ ውሳኔ የሚያሳልፉበት መድረክ በመሆኑ ልምድና ተሞክሮን ለመጋራት ትልቅ ትርጉም እንደሚሰጠው ተናግረዋል። የአየር ንብረት ጉባኤን ለማስተናገድ ጥያቄ የሚያቀርቡ ሀገራት በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሥርዓት የሚያከናወኑት የመሠረተ ልማት ግንባታ ስራና ያስመዘገቡት ስኬት እንደሚታይ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ተከላና የአየር ንብረት ፖሊሲና ስትራቴጂ ትግበራ ያላት ቁርጠኝነት ጉባኤውን ለማስተናገድ ያቀረበችው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ እንዲያገኝ ማድረጉን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የተካሄደው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤና ሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮችን በብቃት የማስተናገድ ልምድና አቅም ለመመረጧ ሌላኛው ዐብይ ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። የፓሪሱን ስምምነት ለመተግበር በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ፖሊሲና ስትራቴጂዎች ታሳቢ ያደረጉ የኢትዮጵያ የልማት ተነሳሽነቶችም በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት የሚወሰዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬቶችም ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የራሱን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝም ተናግረዋል። አረንጓዴ አሻራ የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን በመጠበቅ፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥና የሥራ ዕድል ፈጠራን በመደገፍ ሂደት የኢኮኖሚ ዕድገትን በማስቀጠል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ገልጸዋል። ለአየር ንብረት ተፅዕኖ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታም በ2050 ከካርቦን ልቀት ነፃ የኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት የተያዘውን ግብ ዕውን ለማድረግ ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።
የመዲናዋ የወንዝ ዳር ልማቶች የወንዞች ደህንነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና እያበረከቱ ነው
Nov 20, 2025 236
አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የተከናወኑት የወንዝ ዳር ልማቶች ከህዝብ መዝናኛነታቸው ባሻገር የወንዞች ደህንነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና መጫወታቸውን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ በአዲስ አበባ የፍሳሽ ማስወገጃዎችን ከወንዞች ጋር በማገናኘት ሲፈጠሩ በቆዩ ችግሮች ወንዞች ለብክለት ተጋልጠው ቆይተዋል፡፡ ይህም ወንዞቹ ለሰዎች፣ ለእንስሳትና ለዕፅዋት ጤንነትና ደህንነት ጥቅም ከመስጠት ይልቅ ስጋት እንዲሆኑ አድርጓቸው ቆይቷል፡፡ ይህን ተከትሎ በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት አድማሱን በማስፋት ወደ ወንዝ ዳርቻ ልማት በመሸጋገሩ የወንዞችን ደህንነት ማስጠበቅ ተችሏል፡፡ የወንዝ ዳር ፕሮጀክት መተግበር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የስጋት ምንጭ የነበሩት ወንዞች የመዝናኛ ማዕከል ሆነዋል፡፡ ኢዜአ በወንዝ ዳር ልማቶች በለሙ ቦታዎች ሲዝናኑ ያገኛቸው የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች እንደገለጹት ቦታዎቹ አማራጭ የእረፍት ማሳለፊያ ከመሆናቸው ባሻገር የከተማዋን ገጽታ ውብ አድርገውታል፡፡ አቶ መርሳ በቀለ በወንዞች ዳርቻ የተሰሩ የልማት ስራዎች ከዚህ ቀደም ለማየትም ሆነ በአካባቢው ለማለፍ አስቸጋሪ የነበሩ ቦታዎችን ውብና ጽዱ ያደረጉ ናቸው ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ ወንዞችን ከብክለት ነፃ በማድረግ ደህንነታቸው ተጠብቆ ለህዝብ መዝናኛነት እንዲውሉ ከማስቻል ባለፈ አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብና ጽዱ እንዳደረጓት ገልጸዋል፡፡ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ግርማዬ ፍስሃ በበኩላቸው፤ የከተማዋ ወንዞች የቆሻሻ መጣያ እንደነበሩ አስታውሰው፤ በዚህ ደረጃ ለምተው በመመልከታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ የልማት ስራው ወንዞቹንና በዙሪያቸው ያሉ አካባቢዎችን ውብና ፅዱ ከማድረግ ባሻገር ኢትዮጵያዊያን በአካባቢ ጥበቃ ያላቸውን ልምድና ክህሎት ያሳዩበት መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ ጋዲሳ ዋቅጅራናቸው፡፡ በኮሪደር ልማትና በወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች ለህፃናትና ወጣቶች የሚያገለግሉ ምቹ የሆኑ በርካታ መዝናኛዎች መገንባታቸውን የተናገሩት ወጣት ሰለሞን ዳዊት እና አብዲ መልካሙ ናቸው፡፡ መዝናኛ ቦታዎቹ ጊዜአችንን በአልባሌ ቦታ ከማሳለፍ ይልቅ በመልካም ድባብ በመታጀብ ንፁህ አየር እየወሰድን እንድንዝናና ዕድል ፈጥረውልናል ብለዋል፡፡ የልማት ስራዎቹ ከመዝናኛነት ባለፈ ህብረተሰቡ ስለ አካባቢ ጥበቃና እንክብካቤ ያለው ግንዛቤ እንዲጨምር የሚያስችሉ መሆናቸውን የገለጸው ወጣት ይታያል ደጋጋ ነው ፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 236
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 234
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል።   ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል።   ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ለሱዳን ግጭት ዓለም አቀፍ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል- ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
Nov 19, 2025 345
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የሱዳን ግጭት ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቀናጀ ምላሽ እንዲሰጥ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ያዘጋጀው ሁለተኛ የሱዳን የልዩ ልዑኮች ፎረም ዛሬ በጅቡቲ ተካሄዷል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ተዋንያን ተሳትፈዋል። ፎረሙ በሱዳን ላለው ቀውስ የተቀናጀ መልስ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።   የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር የሱዳን ሰላም በሱዳናውያን የሚመራ፣ ቀጣናዊ ትብብር የተረጋገጠበት እና ዓለም በአንድ ድምጽ የሚደግፈው ሊሆን እንደሚገባ አመልክተዋል። በሱዳን ያለውን ግጭት ለማስቆም፣ ንጹሃን ዜጎችን ለመጠበቅ እና የኢጋድ ቀጣናን የተረጋጋ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ዋና ፀሐፊው ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን በሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደረስ፣ የሰብዓዊ እርዳታ መተላለፊያ እንዲከፈት እና ተአማኒነት ያለው የስልጣን ሽግግር እንዲኖር በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። ኢጋድ ሱዳናውያን በሀገራቸው ሰላም እና ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ክብራቸው እንዲጠበቅ ያላቸው መሻት እንዲሳካ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በመረጃው አመልክቷል።
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 646
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል።   የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 370
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 460
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 529
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 686
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2329
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2480
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3368
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3455
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 1591
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1068
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6890
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5369
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 56965
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52117
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32819
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30332
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26436
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25128
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24740
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 24714
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 56965
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52117
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32819
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30332
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በጥምር ግብርና ስኬት ያስመዘገቡት አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ
Nov 14, 2025 499
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ - ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ጨዛ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ለዘመናት ባከናወኑት የግብርና ልማት ሥራ ኑሯቸው ከእጅ ወደ አፍ የዘለለ አልነበረም። ዛሬ ላይ ሆነው ያን ዘመንና ያሳለፉትን ዕድሜ ሲያስታውሱ ይቆጫሉ። በኋላ ቀር መንገድ ሲያከናውኑት ከነበረው የግብርና ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ መሆንም፤ ሀብት ማፍራትም ሳይችሉ ቀርተዋል።   አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ይባላሉ። ከሰበሰቡት ሰብል ጎተራቸው ሳይጎድል፣ ከእንስሳት እርባታ ስራቸውም ጥገታቸው ሳትነጥፍ ማየት የዘውትር ህልማቸው ነበር። ለም መሬት ይዘው ምርታማ ባለመሆናቸው ሲቸገሩ፣ የሚሰራ ጉልበት ይዘው ማዕዳቸው እየጎደለ የጎልማሳነት ዕድሜ መባቻ ድረስ ችግር ሲፈራረቅባቸው ዓመታትን አሳልፈዋል። ይህ ፍላጎታቸው ሰምሮ፣ ጓሯቸው ለምቶ፣ ቤታቸው ሞልቶና ጥሪት አፍርተው የማየት ውጥናቸው ሳይሳካ ዓመታት ቢቆጠሩም ዛሬ ግን በጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ነገሮች ተቀይረዋል። የዓመታት ምኞታቸውን ማሳካት ጀምረዋል። ከስድስት ዓመታት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ለስኬት እንዲበቁ ከማድረግ ባለፈ በአካባቢያቸው አርአያ የሆኑ አርሶ አደር አድርጓቸዋል። የጥምር ግብርና ስራቸው ለዓመታት ከነበሩበት ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ በማውጣት ለአፍም ለኪስም ሆኗቸዋል። የመንግስት የልማት ትኩረት የሆነው ጥምር ግብርና በውስን መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅንጅት እንዲያለሙ እድል ፍጥሮላቸዋል። በዋናነት በሰብል፣ በእንሰት፣ በፍራፍሬና በእንስሳት እርባታ ላይ አተኩረው እየሰሩ ይገኛሉ። ይህም የአንዱ ክፍተት በሌላው እየተሞለ ውጤታማ ስላደረጋቸው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው። ለቤት ፍጆታ ብቻ ያመርቱ የነበረው የእንሰት ምርትን በማስፋፋት ችግኙንና ተረፈ ምርቱን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጭምር ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያመርቱት ገብስ ለሌሎች አርሶ አደሮች ምሳሌ መሆን ችለዋል።   ዝርያቸው የተሻሻሉ ላሞችን ስለሚያረቡም ወተት ከማጀታቸው አይጠፋም። በጓሯቸው የሚያለሙትን አትክልትና ፍራፍሬ ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ፈጥረዋል። አርሶ አደሩ ከንብ ማነብ ሥራቸውም እንዲሁ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው። ከአካባቢው ስነምህዳር ምክንያት ብዙም ያልተለመደውን ቡና በመትከል ለፍሬ አብቅተዋል። የእሳቸውን ፈለግ የተከተሉ ሌሎች አርሶ አደሮችም ቡና ማልማት ጀምረዋል። በእጅ ያለን ሀብት ወደ ውጤት ለመቀየር ተግቶ መስራትና ጽናት ያስፈለጋል ያሉት አርሶ አደር ወልዴ፣ በግብርና ባለሙያዎች የተደረገላቸው ሙያዊ ድጋፍና የተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ለውጤታቸው ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የእርሻ ልማትና የእንስሳት እርባታውን በቅንጅት ማከናወናቸውም እንዲሁ። አርሶ አደር ወልዴ የዓመታት ቁጭታቸው ዛሬ መፍትሄ እያገኘ ነው። የጥምር ግብርና ሥራቸው በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉና ልጆቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እንዲያሳድጉ አስችሏቸዋል። መኖሪያ ቤትን ጨምሮ የተለያየ ሀብት ለማፍራት ምክንያት በመሆኑም ልማቱን አስፋፍቶ ለማከናወን አቅደዋል።   አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ጭምር አርአያ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙራዱ ብሩ ናቸው። ቀደም ሲል በገብስ ምርት ላይ ብቻ አተኩረው ይሰሩ የነበረውን የግብርና ሥራ እንዲቀይሩ ምክንያት እንደሆኗቸው ይገልጻሉ። ከአርሶ አደር ወልዴ በወሰዱት ልምድ ወደ ጥምር ግብርና ገብተዋል። በዚህም ድርቅ የመቋቋም አቅም ያለውን እንሰት በማሳቸው በስፋት ማልማት ጀምረዋል። የነበሯቸውን ሀገረሰብ የዳልጋ ከብቶች በተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች በመቀየር የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ተግተው እየሰሩ ነው። ጥምር ግብርና የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ከአርሶ አደር ወልዴ ተምሪያለሁ ይላሉ። ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባለፈ የመሬት ለምነትን ለማስጠበቅም ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ የጀመርነውን ሥራ እናጠናክራለን ሲሉም ነው የገለጹት።   የሙህር አክሊል ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ መኑር ጀማል በበኩላቸው "አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ በውስን መሬት ገብስ፣ እንሰት፣ ቡና እና የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በጥምር በማልማት የራሳቸውን ህይወት ከመቀየር ባለፈ ለሌሎች አርሶ አደሮች አርአያ እየሆኑን ነው ብለዋል። አርሶ አደሩ በሽታ መቋቋም የሚችሉና ለመድሃኒትነት የሚፈለጉ የእንሰት ዝርያዎችን በማፍላት ለገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ። ከዚህም ባለፈ በመጥፋት ላይ የነበሩ የእንሰት ዝርያዎችን የመታደግና የአፈር ለምነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውንም ተናግረዋል፡፡ የጥምር ግብርና አሰራር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ በመሆኑ በወረዳው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት። የአርሶ አደር ወልዴ ልምድን በማስፋት የሌሎች አርሶ አደሮችም ጓዳ ሞልቶ እንዲትረፈረፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጥምር ግብርና አርሶ አደሩ ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ጭምር እንዲተርፍ የማድርጉ ሥራ ይጠናከራል ብለዋል።   ልማቱ እርስ በእርስ የሚደጋገፉና በአንድ መሬት ላይ የተለያዩ ምርቶችን በማግኘት የተሻለ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚሰራው ሥራ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ በጥቂት መሬት ብዙ ማምረት መቻል ነው። በመሆኑም በተለይ የመሬት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በሥራ ውጤታማ ለመሆን ሁሉም ነገር ምቹና አልጋ በአልጋ መሆን የግድ እንዳልሆነ አርሶ አደሩ ጥሩ ማሳያ ናቸው። ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ዕድል እንዴት ወደሀብትነት መቀየር እችላለሁ ብለው ከሰሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ የእሳቸው የስኬት ጉዞ በቂ ማሳያ ነው። ሰርቶ ለመለወጥም ሆነ ሀብት ለማፍራት ችግሮችን በጽናት ማለፍ እና የሥራ ትጋት ወሳኝ ነውና ተሞክሯቸውን ማስፋት ያስፈልጋል።
  "ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ"
Nov 12, 2025 474
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ" ብርሃኑ ፍቃዱ -ከሰቆጣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልካዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረት ያለው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ማብራራታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ የባህር በሯን ያጣችበትን የ30 ዓመታት ታሪክ ለመቀልበስ ይህን ያህል ዓመት እንደማይወስድ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ ሕጋዊና ተቋማዊ መሰረት የሌለው የሚያስቆጭ ብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል ስለመሆኑም አንስተዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ እና አቶ አድማሱ ደሳለኝ፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር የተወለዱበት ስፍራ፣ የኖሩበት ቀዬ፣ ያሳደጋቸው ማህበረሰብ ... የዘመናት ትዝታና ትውስታቸው እንደሆነ ይገልጻሉ። ይህን የታሪካቸው አካል የሆነውን የባሕር በር ማጣትም የሁል ጊዜ ፀፀትና እንደ ሰውነት ጥላ አብሮዋቸው የሚዞር እውነታ ነው። ከአካባቢው ርቆ ለሚገኝ ሰው ትውስታውን ሲያወራ ለሌላው ተረት ተረት፤ ለራስ ደግሞ የውስጥ ቁስል ማገርሸት ሆኖ ነው የሚሰማው ይላሉ።   ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብንና የቀይ ባህር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሸፍጥ ማጣቷ በቀይ ባህር ላይ እየዋኙ፣ ውሃ እየተራጩ፣ በዳርቻው ነፋሻማ ስፍራ እየተዝናኑ... ለኖሩት ለእነ መለሰ እና አድማሱ መቼም የማይረሳ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ለአለም ማሕበረሰብ ጥያቄውን ሲያሳውቁ ተደብቆ ለቆየው ትውስታቸው አዲስ ተስፋ እንደሰጣቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ በአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል ለ12 ዓመታት እንዳገለገሉ በትውስታና ቁጭታቸውን ወደ ኋላ ተመልሰው ያወሳሉ። አሁን በሰቆጣ ከተማ የሚኖሩት አቶ መለሰ ይሄይስ ፤ የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ተደማሪ አቅም ነበር በወቅቱ ይላሉ።   ይህን የአሰብ ወደብንና የቀይ ባሕር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሴራ ኢትዮጵያ ስታጣ ይሰሩበት ከነበረው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ስራ አቁመው ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሰቆጣ መምጣታቸውን አውስተዋል። በራሳቸው ላይ ከደረሰባቸው የስራ እና ሃብትና ንብረት ማጣት ፣ እንግልትና ሌሎች ችግሮች በላይ ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተነጠለችበትን ሁኔታ ሲያስቡና ሲያሰላስሉ እንደሚያስቆጫቸው ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን በማጣት የባሕር በር ብቻ ሳይሆን የገቢና ወጭ ንግድን፣ የነዳጅ ማጣሪያ ጭምር ነው ያጣችው ያሉት አቶ መለሰ፤ አሁን ጥያቄው መነሳቱ ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ ገናናነቷ ለመመለስ ያለመ አበረታች ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። መንግስት ያነሳው የባሕር በር ጥያቄም የዘመናት ቁጭታችንን፣ ብስጭታችንን እና ህልማችንን ከተደበቀ ትውስታ፤ ወደ አዲስ ተስፋ የወሰደ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ህጋዊና ታሪካዊ ነው ያሉት አቶ መለሰ ፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝም ለአዲሱ ትውልድ በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።   ከ1973 ዓ.ም ጀምረው ለአስር ተከታታይ ዓመታት በአሰብ ወደብ የሲቪል መሃንዲስ ክፍል ሰራተኛ እንደነበሩ ያወሱት አቶ አድማሱ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የባሕር ባር ባለቤት በሆነችባቸው ዘመናት ገናና እና የተከበረች ሀገር ሆና መቆየቷን አንስተዋል። የባሕር በሩ የኢትዮጵያ የገቢና ወጭ ንግድ የሚሳለጥበት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሄን ታላቅ ትሩፋትና ፀጋ ለማስመለስ የተጀመረው እንቅስቃሴ ቁጭትና ትውስታችንን ወደ አዲስ ተስፋ የቀየረ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪካዊ ጠላቶችና ባንዳዎች እኩይ ሴራ የባሕር በር ካጣች ወዲህ ጥያቄውን ማንሳት የማይቻልበት የአፈናው ዘመን አክትሞ በለውጡ መንግስት መነሳቱ አበረታችና ለማስመለስም ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። እኔም ባለኝ አቅም ሁሉ ስለባሕር ባር አስፈላጊነት፣ ጥቅምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ለስኬታማነቱ የድርሻዬ እወጣለሁ ሲሉም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም