ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮቶችን ለመፍታት እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ ነው
Dec 1, 2025 43
አዲስ አበባ፣ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮቶችን ለመፍታት፣ ተገዢነትን ለማሻሻል እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር መመለስ ላይ በሚታዩ ክፍተቶች ዙሪያ ከቡና፣ ሰሊጥ እና ጥራጥሬ ላኪዎች ጋር ተወያይተዋል። በምክክር መድረኩ ባንኩ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገቢ የመጠበቅ እና የኤክስፖርት ገቢ በወቅቱ እና በግልጸኝነት እንዲመለስ የማድረግ ሃላፊነት እንዳለበት ተጠቁሟል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ከሕጋዊ ርምጃ በፊት ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር ገንቢ ውይይት ማድረግን እንደሚያስቀድም ተጠቅሷል፡፡   በዚህም ባንኩ ተግዳሮቶችን ለመፍታት፣ ተገዢነትን ለማሻሻል እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ባንኩ ከዚህ ባለፈም ተጠያቂነትና ኃላፊነት የሚሰማው የወጪ ንግድ ልምዶችን የማበረታታት እና የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱን የማሳደግ ሥራውን እንደሚያጠናክር ነው የተገለጸው ።
በመዲናዋ የግብር ከፋዮችን ቅሬታ አጣርቶ ምላሽ የሚሰጥ አሰራር ሊጀመር ነው
Dec 1, 2025 41
አዲስ አበባ ፤ ሕዳር 22/2018 ( ኢዜአ) ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግብር ከፋዮችን ቅሬታ ሃላፊዎች በተገኙበት አጣርቶ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አሰራር ከመጪው ሐሙስ ጀምሮ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡ በአዲስ አበባ የግብር አሰባሰብና የገቢዎች አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚኖርን ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በከንቲባ ጽ/ቤት ሥር ተዋቅሯል። አሰራሩ በአስተዳደሩ የገቢዎች ቢሮ ስር በተዘረጋው የቅሬታ አፈታት ሥርዓት ያልረኩ ግብር ከፋዮች ቅሬታዎቻቸውን የሚያቀርቡበት ነው፡፡ በዚህ መሰረትም ከገቢ አሰባሰብ፣ ከሠራተኞች ሥነ ምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር የሚነሱ ቅሬታዎች ዘወትር ሐሙስ ሃላፊዎች በተገኙበት የሚደመጡና ተጣርተው ምላሽ የሚሰጥባቸው ይሆናል፡፡ የተዘረጋው አሰራር ለከንቲባ ጽ/ቤት በሚስጢር ጥቆማ ከሚሰጥበት ነጻ የጥሪ ማዕከል 9977 እና የሚስጢር ሳጥን በተጨማሪ ቅሬታዎችን በአካል ለበላይ አመራር ማቅረብ ያስችላል፡፡ አሰራሩ ከፊታችን ሐሙስ ጀምሮ ወደ ተግባር እንደሚገባ የከተማ አስተዳደሩ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል፡፡ ስለሆነም ከመጪው ሐሙስ ሕዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከገቢዎች ጋር ብቻ የተያያዙ ቅሬታዎችን አመራሩ ተቀብሎ እንደሚያስተናግድ ተጠቁሟል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው-የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች
Dec 1, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡-ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው ሲሉ የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ገለጹ። በአዲስ አበባ የተካሄደው የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም ታላቁ የሕዳሴ ግድብ አስድናቂ የምህንድስና ውጤት መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፥ አፍሪካ በራሷ አቅም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል በማሳየት ትርክት የቀየረ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት በልዩ ጽናትና በራሳቸው አቅም ግድቡን ማሳካታቸው ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ትምህርት የሰጠና የሚደንቅ ደማቅ አሻራ መሆኑን ገልጸዋል። ግድቡ የፅናት፣ የራስን መቻል እና የአህጉራዊ ኩራትና የአንድነት ብርሃን መሆኑንም ተናግረዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሕዝባቸውን በማስተባበር ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት መስጠቱንም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ገንዘባቸውን፣ እውቀታቸውን እና ጉልበታቸውን ሳይሰስቱ ለዓመታት በመትጋት እውን ያደረጉት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካ በራሷ አቅም ታላላቅ ፕሮጀክቶችን እንደምታሳካ ህያው ምስክር ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራሳቸው አቅም ማከናወን አይችሉም የሚለውን የተዛባ ትርክት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሙሉ ለሙሉ መቀልበሱንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የሕዝቧን የተደመረ አቅም በመጠቀም ብሔራዊ ፕሮጀክቷን እውን አድርጋለች ያሉት የሚዲያ ባለሙያዎቹ ፥ ግድቡ አፍሪካውያን ሲተባበሩ የጋራ ህልማቸውን እውን ማድረግ እንደሚችሉ ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካን አቅም፣ ታላቅነትና በልጆቿ ጥረት ግቧን ማሳካት እንደምትችል ህያው ማሳያ መሆኑንም አንስተዋል። ግድቡ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ጉልህ አበርክቶ ያለው መሆኑንም የሚዲያ ባለሙያዎቹ ጠቅሰዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ዋጋ ከፍለው ያሳኩት አህጉራዊ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል። ለመላው አፍሪካውያን የኩራት ምንጭ የሆነው ሕዳሴ ግድብ በአህጉሪቱ አዲስ የይቻላል የለውጥ ጉዞን ያቀጣጠለ መሆኑን ገልጸዋል። የበለጸገችና እና አንድነቷ የጠነከረ አፍሪካን እውን በማድረግ ሂደት ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ጠቁመዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የበርካታ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ መመረቁ ይታወሳል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በጤናው ዘርፍ የመንግስትን ጥረት በማገዝ ረገድ የማህበራዊ ተቋማት ሚና የላቀ ነው
Dec 1, 2025 63
ሀዋሳ ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በጤናው ዘርፍ የመንግስትን ጥረት በማገዝ ረገድ የማህበራዊ ተቋማት ትብብርና ተሳትፎ ሚናው የላቀ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። በሲዳማ ክልል ዳሌ ወረዳ ዋራ ቀበሌ በኢትዮጵያ ሃዋርያት ቤተክርስትያን ከ25 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የጤና ጣቢያን ርዕሰ መስተዳድሩ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) መርቀው ስራ አስጀምረዋል።   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ በጤናው ዘርፍ መከላከልና ማከመን መሰረት በማድረግ መንግስት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   ከገጠር እስከ ከተማ የጤና ተደራሽነትን የማስፋትና የዜጎችን ጤና በመጠበቅ ረገድም ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። የጤና ተቋማትን በብቁና የሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲሁም በቁሳቁስ የማሟላትና የማደራጀት ስራም እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም በጤናው ዘርፍ የመንግስትን ጥረት በማገዝ ረገድ የማህበራዊ ተቋማት ትብብርና ተሳትፎ ሚናው የላቀ መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ አመልክተዋል ።   በዋራ ቀበሌ የተገነባው ጤና ጣቢያ ለአካባቢው ህብረተሰብ የተሟላ የጤና አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ ጤና ቢሮ ጤና ጣቢያውን የተረከበ ሲሆን የላቦራቶሪ፣ ኤክስሬይ፣ አልትራ ሳውንድና ሌሎችም አገልግሎቶችን እንዲሰጥ ተደርጎ በተሟላ ግብአትና የሰው ሃይል ተደራጅቶ ስራ ጀምሯል።   በኢትዮጵያ ሃዋርያት ቤተክርስትያን የተከናወነው ተግባር ለሌሎችም ተምሳሌት በመሆኑ ርእሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።
የሚታይ
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮቶችን ለመፍታት እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ ነው
Dec 1, 2025 43
አዲስ አበባ፣ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮቶችን ለመፍታት፣ ተገዢነትን ለማሻሻል እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር መመለስ ላይ በሚታዩ ክፍተቶች ዙሪያ ከቡና፣ ሰሊጥ እና ጥራጥሬ ላኪዎች ጋር ተወያይተዋል። በምክክር መድረኩ ባንኩ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገቢ የመጠበቅ እና የኤክስፖርት ገቢ በወቅቱ እና በግልጸኝነት እንዲመለስ የማድረግ ሃላፊነት እንዳለበት ተጠቁሟል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ከሕጋዊ ርምጃ በፊት ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር ገንቢ ውይይት ማድረግን እንደሚያስቀድም ተጠቅሷል፡፡   በዚህም ባንኩ ተግዳሮቶችን ለመፍታት፣ ተገዢነትን ለማሻሻል እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ባንኩ ከዚህ ባለፈም ተጠያቂነትና ኃላፊነት የሚሰማው የወጪ ንግድ ልምዶችን የማበረታታት እና የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱን የማሳደግ ሥራውን እንደሚያጠናክር ነው የተገለጸው ።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው-የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች
Dec 1, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡-ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው ሲሉ የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ገለጹ። በአዲስ አበባ የተካሄደው የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም ታላቁ የሕዳሴ ግድብ አስድናቂ የምህንድስና ውጤት መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፥ አፍሪካ በራሷ አቅም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል በማሳየት ትርክት የቀየረ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት በልዩ ጽናትና በራሳቸው አቅም ግድቡን ማሳካታቸው ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ትምህርት የሰጠና የሚደንቅ ደማቅ አሻራ መሆኑን ገልጸዋል። ግድቡ የፅናት፣ የራስን መቻል እና የአህጉራዊ ኩራትና የአንድነት ብርሃን መሆኑንም ተናግረዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሕዝባቸውን በማስተባበር ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት መስጠቱንም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ገንዘባቸውን፣ እውቀታቸውን እና ጉልበታቸውን ሳይሰስቱ ለዓመታት በመትጋት እውን ያደረጉት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካ በራሷ አቅም ታላላቅ ፕሮጀክቶችን እንደምታሳካ ህያው ምስክር ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራሳቸው አቅም ማከናወን አይችሉም የሚለውን የተዛባ ትርክት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሙሉ ለሙሉ መቀልበሱንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የሕዝቧን የተደመረ አቅም በመጠቀም ብሔራዊ ፕሮጀክቷን እውን አድርጋለች ያሉት የሚዲያ ባለሙያዎቹ ፥ ግድቡ አፍሪካውያን ሲተባበሩ የጋራ ህልማቸውን እውን ማድረግ እንደሚችሉ ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካን አቅም፣ ታላቅነትና በልጆቿ ጥረት ግቧን ማሳካት እንደምትችል ህያው ማሳያ መሆኑንም አንስተዋል። ግድቡ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ጉልህ አበርክቶ ያለው መሆኑንም የሚዲያ ባለሙያዎቹ ጠቅሰዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ዋጋ ከፍለው ያሳኩት አህጉራዊ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል። ለመላው አፍሪካውያን የኩራት ምንጭ የሆነው ሕዳሴ ግድብ በአህጉሪቱ አዲስ የይቻላል የለውጥ ጉዞን ያቀጣጠለ መሆኑን ገልጸዋል። የበለጸገችና እና አንድነቷ የጠነከረ አፍሪካን እውን በማድረግ ሂደት ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ጠቁመዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የበርካታ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ መመረቁ ይታወሳል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የገበያ ማዕከላቱ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ለገበያ መረጋጋት ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው
Dec 1, 2025 61
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የተገነቡ ትላልቅ የገበያ ማዕከላት አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ መረጋጋትና ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት በመፍጠር ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑ ተገለጸ። በአዲስ አበባ ከተማ የምርት ፍላጎትና አቅርቦትን በማመጣጠን የፍጆታ ምርቶችን በአንድ ቦታ ለመሸመት አማራጭ የግብይት ማዕከላት አለመኖር ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል። የከተማ አስተዳደሩ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታትና የገበያውን ሁኔታ ለማረጋጋት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ ግዙፍ የገበያ ማዕከላት ግንባታ አንዱ ነው። በገበያ ማዕከላቱ የግብይት ሥርዓቱ ላይ የነበሩ የተንዛዙ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ ሸማቹ በተመጣጣኝ ዋጋ የሚፈልገውን ምርት እንዲያገኝ ዕድል ፈጥረዋል። በከተማዋ መግቢያ በሮች የተገነቡ የገበያ ማዕከላት የምርት አቅርቦትና ፍላጎትን በማጣጣም ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት መፍጠራቸውን ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ሸማቾች፣ ነጋዴዎችና አምራቾች ተናግረዋል።   ሸማች ሙሉነሽ ደምሴ እና ዮሴፍ በቀለ በአቅራቢያቸው የተከፈቱ የገበያ ማዕከላት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እንዳስቻሏቸው ተናግረዋል።   በተለይም የፍጆታ ዕቃዎችን በአንድ ቦታ ላይ ማግኘት መቻላቸው ጊዜና ጉልበት እንደቆጠበላቸው በማንሳት።   በገበያ ማዕከላቱ ምርቶችን የሚያቀርቡ ነጋዴዎች በበኩላቸው ቀደም ሲል የነበረው የግብይት ሰንሰለት የተንዛዛና ለህገወጥነት የተጋለጠ መሆኑን አስታውሰዋል።   በገበያ ማዕከላቱ ከአምራቹ በቀጥታ የሚመጡ ምርቶችን ሸማቹን ማህበረሰብ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ማስቻሉን የተናገሩት ደግሞ ነጋዴ አበራሽ ወልደሩፋኤል እና ሀጂ ሁሴን የሱፍ ናቸው።   ከአምራቾች መካከል ጉርሜሳ ጀልቀባ በገበያ ማዕከላቱ የግብይት እሴት ሰንሰለቱ እንዲያጥር በመደረጉ የተረጋጋ የምርቶች ዋጋ እንዲኖር አስችሏል ነው ያሉት።   የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሀቢባ ሲራጅ በበኩላቸው በከተማዋ የነበሩ አላስፈላጊ የግብይት ሰብሰለቶችን በማስወገድ በከተማዋ መግቢያ በሮች ላይ አምስት ትላልቅ የገበያ ማዕከላት መገንባታቸውን አንስተዋል። ማዕከላቱ አላስፈላጊ የንግድ ሰንሰለትን በማሳጠር አምራቹን ነጋዴውንና ሸማቹን በቀጥታ እንዲገናኙ አድርገዋል ነው ያሉት። ከዚህ ባለፈ በአራት የግብይት ቦታዎች የተጀመረው የቅዳሜና እሁድ ገበያ አሁን ላይ ወደ 219 ከፍ ማለቱ ለገበያ መረጋጋት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ መግቢያ በሮች የተገነቡት 5ቱ ዘመናዊ የገበያ ማዕከላት ላፍቶ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ቁጥር 1፣ ላፍቶ ሁለገብ ገበያ ማዕከል ቁጥር 2 (ዘመናዊ ሀይፐር ማርኬት እና ሁሉንም የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርች ወዘተ በአንድ ማዕከል ያየዘ)፣ ለሚ ኩራ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከል፣ ኮልፌ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከል፣ አቃቂ ቃሊቲ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከላት ናቸው። የገበያ ማዕከላቱ ዘመናዊ የግብይት ስርዓት እንዲኖር በማድረግ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ፍትሃዊ የግብይት ስርዓት እንዲሰፍን እያስቻሉም ይገኛሉ።
ኢትዮጵያውያን የደመቁበት የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ
Dec 1, 2025 99
ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ ተከናውኗል። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ የሽልማት መርሃ ግብሩ የሚዲያ አጋር ሲሆን የሁለት ቀኑን የሽልማት መርሃ ግብር የቀጥታ ስርጭት ሽፋን በመስጠት ለመላው አፍሪካውያን ተደራሽ አድርጓል። የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ(አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ አድርጓል። የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያን ጎብኝተዋል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች ተከናውኗል። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ያስገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ከ94ቱ ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ሶስቱ በተለያዩ ዘርፎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ አሸናፊ በመሆን ሽልማቱን ተቀብሏል። ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ ሽልማቱን የተጎናጸፈው “Climate Intelligence for Survival: IGAD’s Push for Accurate, Actionable Data” በሚል ርዕስ በጻፈው ጽሁፍ ነው። የጋዜጠኛ ጌትነት ጽሁፍ በኢጋድ ቀጣና ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና የሚዳስስ ነው። በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰት ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋዎችና ኢ-ተገማች የአየር ጸባይ ለውጦች ዜጎችን በማፈናቀል እና በቁም እንስሳት ላይ ያደረሱትን ጉዳት ይቃኛል። ትክክለኛ፣ ጊዜውን የጠበቀና ለተግባር ምላሽ የሚያገለግሉ የአየር ንብረት መረጃዎች የማይበገር አቅም ለመገንባትና አደጋዎችን ለመከላከል ያላቸውን ሚናም ተዳሷል። በጽሁፉ ላይ የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያና ትግበራ ማዕከል(ICPAC) የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን በማጠናከር፣ የትንበያ አቅም ማሳደግና የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት የመቋቋም አቅም ላይ እያከናወነ ያለው ስራ ተቀምጧል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች፣ የአንበጣ መንጋ፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብና ሌሎች ፈተናዎችን ለመከላከል ተአማኒነት ያለው የአየር ንብረት መረጃ ወሳኝ መሆኑም ተመላክቷል። በተለይም ኑሯቸው በተለያዩ ወቅቶች ላይ ለተመረኮዙ አርሶ እና አርብቶ አደሮች መረጃው ወሳኝ መሆኑን ያስቀምጣል። ሌላኛው ተሸላሚ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (ኦቢኤ) ጋዜጠኛ ሽመክት ጉግሳ ነው። የተሸለመበት ዘርፍ በኦሮምኛ ቋንቋ በሰራው ፕሮግራም ነው። ፕሮግራሙ ዛፎች ከሰው ህይወት ጋር ያላቸውን ቁርኝት በዋናነት ይቃኛል። መንደርደሪያውን ከዓለም የዛፍ ጠቀሜታና ጥበቃ በማድረግ በኦሮሚያ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ይዳስሳል። ዛፍ መትከል ተፈጥሮና የሰው ልጅን እንዴት እንደሚጠብቅ በተቃራኒው መቁረጥ የሚያደርሰውን ጉዳትም ያስቃኛል። የ21 ደቂቃ ፕሮግራሙ የኦሮሞ ህዝብ በዘመናት መካከል ዛፎችና የደን ሀብቶች እንዲጠበቁ ያደረገው አስተዋጽኦ ተወስቶበታል። በተለይም በገዳ ስርዓት ውስጥ ዛፍን መጠበቅ ያለው ሚና በስፋት ተነስቷል። አንድ ዛፍ ለአራት ሰዎች መኖር መሠረት ይሆናል፤ ዛፍ መቁረጥ አራት ሰዎችን እንዲሞቱ ያደርጋል የሚል የአባገዳ አስተያየትም ተጠቃሽ ነው። አባ ገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ እናቶችና የአካባቢ ማህበረሰቦች ተፈጥሮን ጠብቆ በማቆየት ያላቸው ሚና ቁልፍ እንደሆነ ተመላክቷል። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መስራችና ስራ አስኪያጅ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን(ኢጋድ) የህይወት ዘመን ጋዜጠኝነት ሽልማት ተበርክቶላታል። ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በሬዲዮ ጋዜጠኝነት ግንባር ቀደምና በዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቷንም ኢጋድ ገልጿል። በብሮድካስት ሚዲያው ከ40 ዓመት በላይ የቆየችው ጋዜጠኛ መዓዛ ሸገር ኤፍኤም 102.1ን ከ18 ዓመታት በፊት በማቋቋም በኢትዮጵያ ቀዳሚ የመረጃ እና የመዝናኛ ጣቢያ እንዲሆን ማድረጓ አመልክቷል። ከጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ አበይት ፕሮግራሞች መካከል “ማንን ምን እንጠይቅልዎ?” እና “ሸገር ካፌ” ተጠቃሽ ናቸው። ጋዜጠኛዋ በፕሮግራሞቹ ህዝብን ከመንግስት አገልግሎቶች ጋር በማገናኘትና በማህበራዊ፣ የህግ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ላይ የተመረኮዙ ውይይቶች እንዲካሄዱ መድረክ መፍጠር መቻሏንም ነው የገለጸው። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መሪ ሀሳብ በሆነው የእናንተ ሬዲዮ መዓዛ በጋዜጠኝነት ሙያ ህዝብን ለማገልገልና የኢትዮጵያውያንን ድምጽ ለማጉላት ያላትን ቁርጠኝነት ኢጋድ አድንቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ኢጋድ አመልክቷል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አመራሩ በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል
Dec 1, 2025 87
ሚዛን አማን፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በቤንች ሸኮ እና በወላይታ ዞኖች ያሉትን የልማት አቅሞች በመጠቀም የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋትና የመንግሥት ተግባራትን በቁርጠኝነት ማከናወን ከአመራሩ እንደሚጠበቅ ተገለጸ። "በመደመር መንግሥት ዕይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ በዞኑ ሚዛን አማን ከተማ አጠቃላይ የአመራር ሥልጠና መስጠት ተጀምሯል። በመድረኩ ላይ መልእክት ያስተላለፉት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ ኩድን እንዳሉት፤ የብልጽግና ጉዞ በኅብረተሰቡ ሕይወት ውስጥ ውጤት እያመጣ እንዲቀጥል ብቃት ያለው አመራር መፍጠር ያስፈልጋል። በተለይ የአካባቢ ጸጋን መለየትና የመልማት ዕድልን ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ቁመና ላይ መገኘት ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ ነው ብለዋል።   ለዚህም ፓርቲው የተለያዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን እየሰጠ ሲሆን አሁን ላይ የሚሰጠው ሥልጠና ልማትና የተግባር ውጤታማነት ላይ ያተኮረ መሆኑን ተናግረዋል። ዞኑ ለአግሮ ኢንዱስትሪ ያለው ምቹ ሁኔታ ትርጉም እንዲኖረው የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማስፋፋትና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ተግባርን በስኬት መምራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በተለይም በዞኑ ያለውን የልማት አቅም በመጠቀም የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት ከአመራሩ ይጠበቃል ብለዋል።   በተመሳሳይም በወላይታ ዞን "በመደመር መንግስት እይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የ3ኛ ዙር የአመራሮች ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በመድረኩ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ፤በዞኑ በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ እመርታዊ ለውጦችን ለማስቀጠል የአመራሩን አቅም ማጎልበትና ብቁ አመራር መፍጠር እንደሚገባ ተናግረዋል።   በግብርናና በገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት እና በኢንዱስትሪ አመርቂ ውጤት ለማስመዝገብና ዕድገቱን ለማስቀጠል በአመራሩ መካከል የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት ሊኖር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ትርክትን በማስረጽ ህዝቡ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በቅርበት ተከታትሎ ለመመለስ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም በአጽንኦት ተናግረዋል። በሥልጠናውም ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የተወጣጡ ከአንድ ሺህ 100 በላይ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ ሀገር በመገንባት ሂደት አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት ይገባል
Dec 1, 2025 79
ነቀምቴ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ ሀገር እንዲገነባ አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ተመለከተ። 20ኛው የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በነቀምቴ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ በፓናል ውይይቱ ላይ እንዳሉት፤ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር ወሳኝ ነው። ብሔሮችና ብሔረሰቦች በአንድነት የሚኖሩባት ነቀምቴ በነዋሪዎቿ ተሳትፎ በከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የልማት እቅዶችም በታቀዱት መሰረት እየተተገበሩ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም የከተማው ነዋሪ አንድነቱን አጠናክሮ የአካባቢውን ሰላም እንዲጠብቅና የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ እንዲያስቀጥል የተናገሩት ከንቲባው በተለይም ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ አገር እንዲገነባ አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።   የነቀምቴ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ መሰረት ሀይሉ በበኩላቸው፤ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር በህዝቦች መካከል ፍቅርና መከባበርን በማጎልበት ሕብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጠናከር የጎላ ሚና አለው ብለዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በነቀምቴ ከተማ መከበሩም የህዝቡን የእርስበርስ ትስስር የሚያጠናክር መሆኑንም አስረድተዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የነቀምቴ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ መላኩ ጌታሁን በበኩላቸው፤ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክሩ እሴቶች ላይ በትኩረት በመስራት ለሀገር እድገት መረባረብ ይገባል ብለዋል። የበለፀገች ሀገርን ለቀጣይ ትውልድ ለማውረስ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ሳይደናቀፉ መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተው የከተማው ነዋሪ ሰላሙን መጠበቅ እና አንድነቱን ማጠናከር እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አዘጋጅነት በሆሳዕና ከተማ እንደሚከበር ይታወቃል።
በዓሉ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ አበርክቷል - አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር
Dec 1, 2025 85
ቡሌ ሆራ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል መከበር ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ አበርክቷል ሲሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በምዕራብ ጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ ከተማ በድምቀት ተከብሯል።   በበዓሉ አከባበር ላይ የተገኙት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በወቅቱ እንዳመለከቱት፤ በዓሉ ኢትዮጵያውያን በጋራ ለመኖር የተስማሙበትና በየዓመቱ ባሕላዊ እሴቶቻቸውን በአደባባይ የሚያንጽባርቁበት ነው። ይህም ጠንካራ የፌዴራል ስርዓት እንዲኖር በማድረግ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን እያጠናከረ ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ ማበርከቱን ተናግረዋል። በዓሉ የእርስ በእርስ ትስስርን በሚያጠናክር መልኩ በየደረጃው ተከብሮ ሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሀገር ደረጃ እንደሚከበር አንስተዋል።   የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን በበኩላቸው፤ በዓሉ በክልሉ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና ትስስር በሚያጠናክር መልኩ ሲከበር ቆይቶ ዛሬ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በዓሉ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ባሕልና እሴቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ ሕብረ ብሔራዊ አንድነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ቃላቸውን የሚያድሱበት መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይ በዓሉ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ ሌሎች በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅት መከበሩ ለሀገራዊ ልማት በጋራ በመቆም ዳግም ሕብረት የሚጠናከርበት ነው ብለዋል።   የምዕራብ ጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዱላ ህርባዬ፣ በዞኑ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ያሉትን ፀጋዎች ወደ ልማት በመለወጥ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። በተለይ ቡናን ጨምሮ ሌሎች የቅባት እህሎች እንዲሁም በቁም እንስሳት ምርታማነት ውጤታማ ያደረጉ ተግባራት በዞኑ መከናወናቸውን አንስተዋል። በዓሉ በክልል ደረጃ በዞኑ መከበሩ የአካባቢውን ጸጋ ከማስተዋወቅ ባለፈ የተጀመሩ ልማቶችን ለማጠናከር ድርሻው የጎላ ነው ብለዋል።  
የአብሮነትና የወንድማማችነት እሴቶችን በማጠናከር ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ልንሰራ ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Dec 1, 2025 96
ጋምቤላ፤ ህዳር 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአብሮነትና የወንድማማችነት እሴቶችን በማጠናከር ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ልንሰራ ይገባል ሲሉ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በጋምቤላ ክልል ደረጃ በአኝዋሃ ዞን ዲማ ወረዳ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል።   ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ በክብረ በዓሉ ላይ እንዳሉት ህገ መንግስቱ ለብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ያጎናፀፈውን መብት በመጠቀም የክልሉን ህዝብ የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በዓሉን ስናከብርም የህዝቦችን አንድነትና ወንድማማችነት የሚሸረሽሩ እንቅስቃሴዎችን በመታገልና የህዝቦችን አንድነትና አብሮነትን በማፅናት ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል። በክልሉ እያጋጠሙ ያሉ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር የተያዘውን የብልጽግና ጉዞ ዕውን ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል። በብዝሃነት ውስጥ ያለውን አንድነት በማጠናከር የክልሉን ህዝብ ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ጥረቶች እንደሚጠናከሩም አብራርተዋል። በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችም ክልሉ ለጀመራቸው የዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች መሳካት ግንባር ቀደም ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሯ አስገንዝበዋል።   የክልሉ ምክር ቤት አፈ -ጉባኤ ወይዘሮ መሠረት ማቲዎስ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በዓሉ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ህገ-መንግስታዊ ዋስትና ያገኙበት ዕለት በመሆኑ ለክልሉ ህዝብ ልዩ ትርጉም አለው። ጋምቤላ የክልሉ ህዝቦች ተቻችለውና ተከባብረው በፍቅር አብረው የሚኖሩበት አካባቢ እንደመሆኑ መጠን ይህንን የጋራ እሴቶች ጠብቆ ለትውልዱ ማስተላለፍ ይጠበቅብናል ብለዋል። በክልል ደረጃ ህገ መንግስቱ የፀደቀበትን ዕለት በዚህ መልኩ በድምቀት ማክበራችን የህዝቦችን አንድነትና እኩልነት አጉልቶ ያሳያል ብለዋል። ከበዓሉ ታዳሚዎች መካከል ወይዘሮ አጁሉ ቶማስ በሰጡት አስተያየት በዓሉን የክልሉ ብሄሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በጋራ ማክበራችን አብሮነታችንና አንድነታችንን ይበልጥ ያጠናክራል ብለዋል። በዓሉ አንዱ የሌላውን ማንነት፣ ወግና እሴት እንድናውቅ እድል የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ ለክልሉ ሰላምና ልማት መሳካት አበርክቶው የጎላ ነው ያሉት ደግሞ ሌላው የበዓሉ ታዳሚ አቶ ቱት ኒውት ናቸው። ትናንት በሲምፖዚየም የተከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በጋምቤላ ክልል ደረጃ በአኝዋሃ ዞን ዲማ ወረዳ እለቱን በሚያደምቁ መርሃ ግብሮች ተከብሮ ውሏል።
መደመራዊ የዝላይ የሽግግር ሂደት ሦስት ቁልፍ ነገሮችን ይይዛል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Nov 30, 2025 264
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 21/2018 (ኢዜአ)፡- መደመራዊ የዝላይ የሽግግር ሂደት ወደ ውጤት መቀየር፣ ወደ ሌላ መሻገር እና ወደ ፊት መስፈንጠር የተሰኙ ቁልፍ ጉዳዮችን እንደሚይዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ መደመራዊ የዝላይ መንገድ ሁለት ዋና ዋና ዓላማዎች እንዳሉት ጠቅሰው፤ አንደኛው ከቀዳሚው ጋር ያለ ልዩነትን በፍጥነት ማጥበብ ሲሆን ሁለተኛው እመርታዊ እድገት ማምጣት መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት መደመራዊ የዝላይ መንገድ ሌሎች የረገጡትን ሁሉ መርገጥ ተገቢ እንዳልሆነ፤ ውጤት ዐይተን ከዚያ መማር እንችላለን ብሎ እንደሚያነሳ ጠቁመዋል። ጊዜ ወሳጅነትንና የአርፋጅነት ፈተናን ማሸነፊያ መሆን አለበት፤ ከሌሎች ውድቀትና ስኬት መማር፣ ከሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ መማር ያስፈልጋል ብሎ እንደሚያምንም አመላክተዋል።   ነገር ግን እያንዳንዱን ዱካ መከተል ውጤታማ አያደርግም ብሎ ያነሳል ብለዋል። በአጠቃላይ መደመራዊ የዝላይ የሽግግር ሂደት ሦስት ቁልፍ ነገሮችን እንደሚይዝ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ እነሱም ወደ ውጤት መቀየር፣ ወደ ሌላ መሻገር እና ወደ ፊት መስፈንጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ይህ ማለትም ነባር ዐቅሞችን ወደ ውጤት መቀየር፣ አዳዲስ ዘርፎች መፍጠር ወደዚያ መሻገር፣ በዘርፎች ውስጥም የሚፈጠር ሽግሽግን መከወን፣ አዳዲስ የመልማት ዐቅሞች ማውጣት፣ አዳዲስ የገበያ ዕድሎች መፍጠርን እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። አክለውም፤ ያለንን ዐቅም ማዘመን፣ ወደ ዓለም መስፈንጠር፣ መዋቅራዊ ሽግግግር ማረጋገጥ፣ ዕውቀትን እንደ ምርት መጠቀም ብሎም ከፈተና ውስጥ ሊፈለቀቅ የሚችል ዕድል ካለ ችግርን ወደ ዕድል መቀየር ይጠበቃል ሲሉ አስረድተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል። በክፍል ሁለት ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል…
Nov 30, 2025 171
  የሀገራዊ ብልጽግና አእማዶች የተባሉት ኢኮኖሚ (ከሁሉም ለሁሉም በሁሉም)፣ ፖለቲካ (አካታችና አሳታፊ) እና ማኅበራዊ (ትውልዳዊ ልማት) ናቸው። በችግር ትብታብ ታስረን እንዳንቀር ተስፈንጥረን ወደምንፈልገው ነገር እንድንደርስ በአንዳንድ ጉዳይ ላይ መደመራዊ ዝላይ አስፈላጊ ነው። መደመራዊ የዝላይ መንገድ ዋና ዋና ዓላማዎች ከቀዳሚው ጋር ያለ ልዩነትን በፍጥነት ማጥበብ እና እመርታዊ እድገት ማምጣት ናቸው። የትውልድ ግንባታ ስትራቴጂዎች የሚባሉት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ ዲጂታል ዓርበኝነት፣ የትምህርት ተሃድሶ እና የባህል ኢንዱስትሪ ናቸው። ማስተካከል፣ ማስፋፋት እና ማበርከት የመደመር ትውልድ መርሆዎች ናቸው። የመደመር መንግሥት እንቅፋት - ሐሳብ አልቦነት ነው። ሐሳብ አልቦነት ማለትም በሕዝበኝነት መታወር እና መስከር፤ በነባር ባህል መታጠርና መታሰር ፤ በጊዜያዊ ችግር መሸበርና መሰበር ማለት ነው። የሐሳብ ሉዓላዊነት- የመደመር አሸናፊነት ነው።በዚህም መሠረት አመክኗዊ ውይይትና ሙግት፣ ሚዛናዊ ትብብርና ፉክክር፣ ሐሳብን በወረቀት - ሥራን በመሬት መሆን አለበት። ፍሪሊዮን - የመደመር ቀመር ነው። ይህ ማለትም መስጠትና አገልግሎት፣ ሰውን ማትረፍና ማብቃት፣ ወደ ሰላምና ብልጽግና፣ ስለ ሀገርና ትውልድ እንዲሁም ሐሳብና ሰው በተቋም ማለት ነው።
ፖለቲካ
የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አመራሩ በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል
Dec 1, 2025 87
ሚዛን አማን፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በቤንች ሸኮ እና በወላይታ ዞኖች ያሉትን የልማት አቅሞች በመጠቀም የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋትና የመንግሥት ተግባራትን በቁርጠኝነት ማከናወን ከአመራሩ እንደሚጠበቅ ተገለጸ። "በመደመር መንግሥት ዕይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ በዞኑ ሚዛን አማን ከተማ አጠቃላይ የአመራር ሥልጠና መስጠት ተጀምሯል። በመድረኩ ላይ መልእክት ያስተላለፉት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ ኩድን እንዳሉት፤ የብልጽግና ጉዞ በኅብረተሰቡ ሕይወት ውስጥ ውጤት እያመጣ እንዲቀጥል ብቃት ያለው አመራር መፍጠር ያስፈልጋል። በተለይ የአካባቢ ጸጋን መለየትና የመልማት ዕድልን ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ቁመና ላይ መገኘት ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ ነው ብለዋል።   ለዚህም ፓርቲው የተለያዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን እየሰጠ ሲሆን አሁን ላይ የሚሰጠው ሥልጠና ልማትና የተግባር ውጤታማነት ላይ ያተኮረ መሆኑን ተናግረዋል። ዞኑ ለአግሮ ኢንዱስትሪ ያለው ምቹ ሁኔታ ትርጉም እንዲኖረው የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማስፋፋትና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ተግባርን በስኬት መምራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በተለይም በዞኑ ያለውን የልማት አቅም በመጠቀም የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት ከአመራሩ ይጠበቃል ብለዋል።   በተመሳሳይም በወላይታ ዞን "በመደመር መንግስት እይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የ3ኛ ዙር የአመራሮች ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በመድረኩ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ፤በዞኑ በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ እመርታዊ ለውጦችን ለማስቀጠል የአመራሩን አቅም ማጎልበትና ብቁ አመራር መፍጠር እንደሚገባ ተናግረዋል።   በግብርናና በገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት እና በኢንዱስትሪ አመርቂ ውጤት ለማስመዝገብና ዕድገቱን ለማስቀጠል በአመራሩ መካከል የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት ሊኖር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ትርክትን በማስረጽ ህዝቡ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በቅርበት ተከታትሎ ለመመለስ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም በአጽንኦት ተናግረዋል። በሥልጠናውም ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የተወጣጡ ከአንድ ሺህ 100 በላይ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ ሀገር በመገንባት ሂደት አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት ይገባል
Dec 1, 2025 79
ነቀምቴ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ ሀገር እንዲገነባ አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ተመለከተ። 20ኛው የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በነቀምቴ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ በፓናል ውይይቱ ላይ እንዳሉት፤ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር ወሳኝ ነው። ብሔሮችና ብሔረሰቦች በአንድነት የሚኖሩባት ነቀምቴ በነዋሪዎቿ ተሳትፎ በከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የልማት እቅዶችም በታቀዱት መሰረት እየተተገበሩ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም የከተማው ነዋሪ አንድነቱን አጠናክሮ የአካባቢውን ሰላም እንዲጠብቅና የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ እንዲያስቀጥል የተናገሩት ከንቲባው በተለይም ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ አገር እንዲገነባ አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።   የነቀምቴ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ መሰረት ሀይሉ በበኩላቸው፤ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር በህዝቦች መካከል ፍቅርና መከባበርን በማጎልበት ሕብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጠናከር የጎላ ሚና አለው ብለዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በነቀምቴ ከተማ መከበሩም የህዝቡን የእርስበርስ ትስስር የሚያጠናክር መሆኑንም አስረድተዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የነቀምቴ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ መላኩ ጌታሁን በበኩላቸው፤ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክሩ እሴቶች ላይ በትኩረት በመስራት ለሀገር እድገት መረባረብ ይገባል ብለዋል። የበለፀገች ሀገርን ለቀጣይ ትውልድ ለማውረስ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ሳይደናቀፉ መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተው የከተማው ነዋሪ ሰላሙን መጠበቅ እና አንድነቱን ማጠናከር እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አዘጋጅነት በሆሳዕና ከተማ እንደሚከበር ይታወቃል።
በዓሉ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ አበርክቷል - አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር
Dec 1, 2025 85
ቡሌ ሆራ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል መከበር ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ አበርክቷል ሲሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በምዕራብ ጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ ከተማ በድምቀት ተከብሯል።   በበዓሉ አከባበር ላይ የተገኙት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በወቅቱ እንዳመለከቱት፤ በዓሉ ኢትዮጵያውያን በጋራ ለመኖር የተስማሙበትና በየዓመቱ ባሕላዊ እሴቶቻቸውን በአደባባይ የሚያንጽባርቁበት ነው። ይህም ጠንካራ የፌዴራል ስርዓት እንዲኖር በማድረግ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን እያጠናከረ ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ ማበርከቱን ተናግረዋል። በዓሉ የእርስ በእርስ ትስስርን በሚያጠናክር መልኩ በየደረጃው ተከብሮ ሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሀገር ደረጃ እንደሚከበር አንስተዋል።   የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን በበኩላቸው፤ በዓሉ በክልሉ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና ትስስር በሚያጠናክር መልኩ ሲከበር ቆይቶ ዛሬ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በዓሉ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ባሕልና እሴቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ ሕብረ ብሔራዊ አንድነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ቃላቸውን የሚያድሱበት መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይ በዓሉ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ ሌሎች በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅት መከበሩ ለሀገራዊ ልማት በጋራ በመቆም ዳግም ሕብረት የሚጠናከርበት ነው ብለዋል።   የምዕራብ ጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዱላ ህርባዬ፣ በዞኑ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ያሉትን ፀጋዎች ወደ ልማት በመለወጥ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። በተለይ ቡናን ጨምሮ ሌሎች የቅባት እህሎች እንዲሁም በቁም እንስሳት ምርታማነት ውጤታማ ያደረጉ ተግባራት በዞኑ መከናወናቸውን አንስተዋል። በዓሉ በክልል ደረጃ በዞኑ መከበሩ የአካባቢውን ጸጋ ከማስተዋወቅ ባለፈ የተጀመሩ ልማቶችን ለማጠናከር ድርሻው የጎላ ነው ብለዋል።  
የአብሮነትና የወንድማማችነት እሴቶችን በማጠናከር ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ልንሰራ ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Dec 1, 2025 96
ጋምቤላ፤ ህዳር 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአብሮነትና የወንድማማችነት እሴቶችን በማጠናከር ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ልንሰራ ይገባል ሲሉ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በጋምቤላ ክልል ደረጃ በአኝዋሃ ዞን ዲማ ወረዳ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል።   ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ በክብረ በዓሉ ላይ እንዳሉት ህገ መንግስቱ ለብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ያጎናፀፈውን መብት በመጠቀም የክልሉን ህዝብ የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በዓሉን ስናከብርም የህዝቦችን አንድነትና ወንድማማችነት የሚሸረሽሩ እንቅስቃሴዎችን በመታገልና የህዝቦችን አንድነትና አብሮነትን በማፅናት ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል። በክልሉ እያጋጠሙ ያሉ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር የተያዘውን የብልጽግና ጉዞ ዕውን ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል። በብዝሃነት ውስጥ ያለውን አንድነት በማጠናከር የክልሉን ህዝብ ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ጥረቶች እንደሚጠናከሩም አብራርተዋል። በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችም ክልሉ ለጀመራቸው የዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች መሳካት ግንባር ቀደም ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሯ አስገንዝበዋል።   የክልሉ ምክር ቤት አፈ -ጉባኤ ወይዘሮ መሠረት ማቲዎስ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በዓሉ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ህገ-መንግስታዊ ዋስትና ያገኙበት ዕለት በመሆኑ ለክልሉ ህዝብ ልዩ ትርጉም አለው። ጋምቤላ የክልሉ ህዝቦች ተቻችለውና ተከባብረው በፍቅር አብረው የሚኖሩበት አካባቢ እንደመሆኑ መጠን ይህንን የጋራ እሴቶች ጠብቆ ለትውልዱ ማስተላለፍ ይጠበቅብናል ብለዋል። በክልል ደረጃ ህገ መንግስቱ የፀደቀበትን ዕለት በዚህ መልኩ በድምቀት ማክበራችን የህዝቦችን አንድነትና እኩልነት አጉልቶ ያሳያል ብለዋል። ከበዓሉ ታዳሚዎች መካከል ወይዘሮ አጁሉ ቶማስ በሰጡት አስተያየት በዓሉን የክልሉ ብሄሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በጋራ ማክበራችን አብሮነታችንና አንድነታችንን ይበልጥ ያጠናክራል ብለዋል። በዓሉ አንዱ የሌላውን ማንነት፣ ወግና እሴት እንድናውቅ እድል የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ ለክልሉ ሰላምና ልማት መሳካት አበርክቶው የጎላ ነው ያሉት ደግሞ ሌላው የበዓሉ ታዳሚ አቶ ቱት ኒውት ናቸው። ትናንት በሲምፖዚየም የተከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በጋምቤላ ክልል ደረጃ በአኝዋሃ ዞን ዲማ ወረዳ እለቱን በሚያደምቁ መርሃ ግብሮች ተከብሮ ውሏል።
መደመራዊ የዝላይ የሽግግር ሂደት ሦስት ቁልፍ ነገሮችን ይይዛል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Nov 30, 2025 264
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 21/2018 (ኢዜአ)፡- መደመራዊ የዝላይ የሽግግር ሂደት ወደ ውጤት መቀየር፣ ወደ ሌላ መሻገር እና ወደ ፊት መስፈንጠር የተሰኙ ቁልፍ ጉዳዮችን እንደሚይዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ መደመራዊ የዝላይ መንገድ ሁለት ዋና ዋና ዓላማዎች እንዳሉት ጠቅሰው፤ አንደኛው ከቀዳሚው ጋር ያለ ልዩነትን በፍጥነት ማጥበብ ሲሆን ሁለተኛው እመርታዊ እድገት ማምጣት መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት መደመራዊ የዝላይ መንገድ ሌሎች የረገጡትን ሁሉ መርገጥ ተገቢ እንዳልሆነ፤ ውጤት ዐይተን ከዚያ መማር እንችላለን ብሎ እንደሚያነሳ ጠቁመዋል። ጊዜ ወሳጅነትንና የአርፋጅነት ፈተናን ማሸነፊያ መሆን አለበት፤ ከሌሎች ውድቀትና ስኬት መማር፣ ከሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ መማር ያስፈልጋል ብሎ እንደሚያምንም አመላክተዋል።   ነገር ግን እያንዳንዱን ዱካ መከተል ውጤታማ አያደርግም ብሎ ያነሳል ብለዋል። በአጠቃላይ መደመራዊ የዝላይ የሽግግር ሂደት ሦስት ቁልፍ ነገሮችን እንደሚይዝ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ እነሱም ወደ ውጤት መቀየር፣ ወደ ሌላ መሻገር እና ወደ ፊት መስፈንጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ይህ ማለትም ነባር ዐቅሞችን ወደ ውጤት መቀየር፣ አዳዲስ ዘርፎች መፍጠር ወደዚያ መሻገር፣ በዘርፎች ውስጥም የሚፈጠር ሽግሽግን መከወን፣ አዳዲስ የመልማት ዐቅሞች ማውጣት፣ አዳዲስ የገበያ ዕድሎች መፍጠርን እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። አክለውም፤ ያለንን ዐቅም ማዘመን፣ ወደ ዓለም መስፈንጠር፣ መዋቅራዊ ሽግግግር ማረጋገጥ፣ ዕውቀትን እንደ ምርት መጠቀም ብሎም ከፈተና ውስጥ ሊፈለቀቅ የሚችል ዕድል ካለ ችግርን ወደ ዕድል መቀየር ይጠበቃል ሲሉ አስረድተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል። በክፍል ሁለት ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል…
Nov 30, 2025 171
  የሀገራዊ ብልጽግና አእማዶች የተባሉት ኢኮኖሚ (ከሁሉም ለሁሉም በሁሉም)፣ ፖለቲካ (አካታችና አሳታፊ) እና ማኅበራዊ (ትውልዳዊ ልማት) ናቸው። በችግር ትብታብ ታስረን እንዳንቀር ተስፈንጥረን ወደምንፈልገው ነገር እንድንደርስ በአንዳንድ ጉዳይ ላይ መደመራዊ ዝላይ አስፈላጊ ነው። መደመራዊ የዝላይ መንገድ ዋና ዋና ዓላማዎች ከቀዳሚው ጋር ያለ ልዩነትን በፍጥነት ማጥበብ እና እመርታዊ እድገት ማምጣት ናቸው። የትውልድ ግንባታ ስትራቴጂዎች የሚባሉት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ ዲጂታል ዓርበኝነት፣ የትምህርት ተሃድሶ እና የባህል ኢንዱስትሪ ናቸው። ማስተካከል፣ ማስፋፋት እና ማበርከት የመደመር ትውልድ መርሆዎች ናቸው። የመደመር መንግሥት እንቅፋት - ሐሳብ አልቦነት ነው። ሐሳብ አልቦነት ማለትም በሕዝበኝነት መታወር እና መስከር፤ በነባር ባህል መታጠርና መታሰር ፤ በጊዜያዊ ችግር መሸበርና መሰበር ማለት ነው። የሐሳብ ሉዓላዊነት- የመደመር አሸናፊነት ነው።በዚህም መሠረት አመክኗዊ ውይይትና ሙግት፣ ሚዛናዊ ትብብርና ፉክክር፣ ሐሳብን በወረቀት - ሥራን በመሬት መሆን አለበት። ፍሪሊዮን - የመደመር ቀመር ነው። ይህ ማለትም መስጠትና አገልግሎት፣ ሰውን ማትረፍና ማብቃት፣ ወደ ሰላምና ብልጽግና፣ ስለ ሀገርና ትውልድ እንዲሁም ሐሳብና ሰው በተቋም ማለት ነው።
ማህበራዊ
በጤናው ዘርፍ የመንግስትን ጥረት በማገዝ ረገድ የማህበራዊ ተቋማት ሚና የላቀ ነው
Dec 1, 2025 63
ሀዋሳ ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በጤናው ዘርፍ የመንግስትን ጥረት በማገዝ ረገድ የማህበራዊ ተቋማት ትብብርና ተሳትፎ ሚናው የላቀ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። በሲዳማ ክልል ዳሌ ወረዳ ዋራ ቀበሌ በኢትዮጵያ ሃዋርያት ቤተክርስትያን ከ25 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የጤና ጣቢያን ርዕሰ መስተዳድሩ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) መርቀው ስራ አስጀምረዋል።   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ በጤናው ዘርፍ መከላከልና ማከመን መሰረት በማድረግ መንግስት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   ከገጠር እስከ ከተማ የጤና ተደራሽነትን የማስፋትና የዜጎችን ጤና በመጠበቅ ረገድም ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። የጤና ተቋማትን በብቁና የሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲሁም በቁሳቁስ የማሟላትና የማደራጀት ስራም እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም በጤናው ዘርፍ የመንግስትን ጥረት በማገዝ ረገድ የማህበራዊ ተቋማት ትብብርና ተሳትፎ ሚናው የላቀ መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ አመልክተዋል ።   በዋራ ቀበሌ የተገነባው ጤና ጣቢያ ለአካባቢው ህብረተሰብ የተሟላ የጤና አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ ጤና ቢሮ ጤና ጣቢያውን የተረከበ ሲሆን የላቦራቶሪ፣ ኤክስሬይ፣ አልትራ ሳውንድና ሌሎችም አገልግሎቶችን እንዲሰጥ ተደርጎ በተሟላ ግብአትና የሰው ሃይል ተደራጅቶ ስራ ጀምሯል።   በኢትዮጵያ ሃዋርያት ቤተክርስትያን የተከናወነው ተግባር ለሌሎችም ተምሳሌት በመሆኑ ርእሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።
በክልሉ ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል
Dec 1, 2025 62
ወልቂጤ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ተናገሩ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀንን በማስመልከት የተዘጋጀ ኤግዚቢሽን እና ባዛር በወልቂጤ ከተማ ተከፍቷል።   ርዕሰ መስተዳድሩ ኤግዚቢሽንና ባዛሩን በከፈቱበት ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በዓሉን የምናከብረው የህዝቦችን አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ እህትማማችነት እና አብሮነትን በማፅናት ነው ብለዋል። ዘንድሮ ለ20ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በክልሉ በዞኖችና በልዩ ወረዳዎች በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር መቆየቱንም ጠቁመዋል። እንደ ሃገር በክልሉ ሆሳዕና ከተማ ''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት ''በሚል መሪ ሀሳብ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን በድምቀት ለማክበር ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።   በዓሉ ሀገራዊና ክልላዊ መግባባትን ለማጠናከር በህዝቦች መካከል ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ለማጎልበት የሚያግዙ የአብሮነት እሴቶችን የምናጠናክርበት ነው ብለዋል። የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው፤ በዓሉ የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ባህላዊ እሴቶች አጉልቶ ለማሳየትና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ረገድ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል። ዞኑ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች ተከባብረው በፍቅር አብረው የሚኖሩበት እንደመሆኑ መጠን በከተማው ባዛርና ኤግዚቢሽን የጋራ እሴቶችን ለማሳየት እንደተዘጋጀም አስረድተዋል።   በስነ-ስርዓቱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎን ጨምሮ የክልሉ የብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ እንዲሁም ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል። በኤግዚቢሽኑና ባዛሩ ላይ ከ200 በላይ የተለያዩ ምርቶች መቅረባቸው የተጠቆመ ሲሆን ከዛሬ ህዳር 22/2018 ዓ.ም እስከ ህዳር 27 /2018 ዓ.ም እንደሚቆይም ተመልክቷል።
የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Dec 1, 2025 105
ደብረ ብርሃን/ ኮምቦልቻ ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የፖሊስ ሰራዊትን አቅም በመገንባት የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ሰላምን ለማፅናት የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገለጸ። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በደብረብርሃን እና ኮምቦልቻ ከተሞች በተቋማዊ ሪፎርም አፈፃፀም፣ በጂኦ ስትራቴጂና የፖሊስ አመራር አቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ መድረክ እያካሄደ ነው። በደብረብርሃን በተካሄደ መድረክ በጠቅላይ መምሪያው የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል አበበ ውቤ ፤ የፖሊስ አባላቱ ፀጥታን በማስከበር ልማትና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን የበኩላቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።   በዚህም በክልሉ ሕግና ፍትህን ለማረጋገጥ በቅንጅት በመስራት የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች እንዲመለሱ እየተደረገ መሆኑን አክለዋል። በክልሉ በተደረገው የፖሊስ ሪፎርም በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መቻሉን አመልክተው፤ ይህም የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና የተጀመረው ስልጠናም የፖሊስን አቅም ይበልጥ የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸዋል። በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በበኩላቸው፤ የባዳና የባንዳዎችን እኩይ ሴራ በማምከን ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል።   የፖሊስ አባላቱ ከስልጠናው የሚያገኙትን እውቀት በመጠቀም የበለጠ እንዲሰሩም አሳስበዋል። የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት፤ መንግስት የልማት ፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን እያቀላጠፈ መሆኑን ገልጸዋል።   ይህንን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል የፖሊስ አባላት ሕግን በማስከበር ሰላምን ለማፅናት የሚሰጣቸውን የአቅም ግንባታ ስልጠና ወደ ተግባር በማሸጋገር ሚናቸውን በብቃት መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። በደቡብ ወሎ ዞን ኮምቦልቻ በተካሄደው መድረክ የተገኙት በአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የጄኔራል ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር የሽወርቅ ላቀው እንደገለጹት፤ በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ከሕብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው። የፖሊስ ተቋማትን በቴክኖሎጂ በማዘመንና በሪፎርም በማደራጀት የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ሰላምን ለማፅናት የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል። የፀጥታ አመራርና አባላትን እውቀትና ክህሎት በማሳደግ ውጤታማ ለማድረግ በየደረጃው ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን አብራርተዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር አሳምን ሙላት በበኩላቸው፤ በዞኑ የሰፈነውን ሰላም በማፅናት የልማት ስራዎች በሕብረተሰቡ ተሳትፎ ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል።   ዛሬ የተጀመረው ስልጠናም እውቀትና ክህሎታችንን በማሳደግ የተሻለ እንድንሰራ እድል ይፈጥርልናል ብለዋል። በስነ ምግባር የታነፅ ብቁ የፖሊስ አመራርና አባላት በመፍጠር የዞኑን ሰላም ለማፅናት በየደረጃው ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ፋንቱ ተጋፋው ናቸው።   በዚህም አበረታች ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው፤ ይህንን ውጤት አስጠብቆ ለማስቀጠል ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ጌታቸው ሙህዬ ፤ ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት የከተማውን ሰላም መጠበቅ በመቻሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ እንዲስፋፋ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል። ሕግን በማስከበር የከተማውን ሰላም አፅንቶ ልማትን ለማስቀጠል ስልጠናው እንደሚረዳቸው ተናግረዋል።   በሁለቱ ከተሞች እየተሰጠ ባለው ስልጠና ከሰሜን ሸዋ ፣ ፣ ከደቡብና ሰሜን ወሎ ዞኖች ፣ ከኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ ከዋግ ኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ፣ ከደብረብርሃን ፣ ከወልዲያ፣ ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ የፀጥታ አመራሮችና አባላት እየተሳተፉ ነው።
ኢኮኖሚ
ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮቶችን ለመፍታት እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ ነው
Dec 1, 2025 43
አዲስ አበባ፣ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮቶችን ለመፍታት፣ ተገዢነትን ለማሻሻል እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር መመለስ ላይ በሚታዩ ክፍተቶች ዙሪያ ከቡና፣ ሰሊጥ እና ጥራጥሬ ላኪዎች ጋር ተወያይተዋል። በምክክር መድረኩ ባንኩ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገቢ የመጠበቅ እና የኤክስፖርት ገቢ በወቅቱ እና በግልጸኝነት እንዲመለስ የማድረግ ሃላፊነት እንዳለበት ተጠቁሟል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ከሕጋዊ ርምጃ በፊት ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር ገንቢ ውይይት ማድረግን እንደሚያስቀድም ተጠቅሷል፡፡   በዚህም ባንኩ ተግዳሮቶችን ለመፍታት፣ ተገዢነትን ለማሻሻል እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ባንኩ ከዚህ ባለፈም ተጠያቂነትና ኃላፊነት የሚሰማው የወጪ ንግድ ልምዶችን የማበረታታት እና የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱን የማሳደግ ሥራውን እንደሚያጠናክር ነው የተገለጸው ።
በመዲናዋ የግብር ከፋዮችን ቅሬታ አጣርቶ ምላሽ የሚሰጥ አሰራር ሊጀመር ነው
Dec 1, 2025 41
አዲስ አበባ ፤ ሕዳር 22/2018 ( ኢዜአ) ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግብር ከፋዮችን ቅሬታ ሃላፊዎች በተገኙበት አጣርቶ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አሰራር ከመጪው ሐሙስ ጀምሮ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡ በአዲስ አበባ የግብር አሰባሰብና የገቢዎች አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚኖርን ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በከንቲባ ጽ/ቤት ሥር ተዋቅሯል። አሰራሩ በአስተዳደሩ የገቢዎች ቢሮ ስር በተዘረጋው የቅሬታ አፈታት ሥርዓት ያልረኩ ግብር ከፋዮች ቅሬታዎቻቸውን የሚያቀርቡበት ነው፡፡ በዚህ መሰረትም ከገቢ አሰባሰብ፣ ከሠራተኞች ሥነ ምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር የሚነሱ ቅሬታዎች ዘወትር ሐሙስ ሃላፊዎች በተገኙበት የሚደመጡና ተጣርተው ምላሽ የሚሰጥባቸው ይሆናል፡፡ የተዘረጋው አሰራር ለከንቲባ ጽ/ቤት በሚስጢር ጥቆማ ከሚሰጥበት ነጻ የጥሪ ማዕከል 9977 እና የሚስጢር ሳጥን በተጨማሪ ቅሬታዎችን በአካል ለበላይ አመራር ማቅረብ ያስችላል፡፡ አሰራሩ ከፊታችን ሐሙስ ጀምሮ ወደ ተግባር እንደሚገባ የከተማ አስተዳደሩ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል፡፡ ስለሆነም ከመጪው ሐሙስ ሕዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከገቢዎች ጋር ብቻ የተያያዙ ቅሬታዎችን አመራሩ ተቀብሎ እንደሚያስተናግድ ተጠቁሟል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው-የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች
Dec 1, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡-ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው ሲሉ የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ገለጹ። በአዲስ አበባ የተካሄደው የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም ታላቁ የሕዳሴ ግድብ አስድናቂ የምህንድስና ውጤት መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፥ አፍሪካ በራሷ አቅም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል በማሳየት ትርክት የቀየረ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት በልዩ ጽናትና በራሳቸው አቅም ግድቡን ማሳካታቸው ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ትምህርት የሰጠና የሚደንቅ ደማቅ አሻራ መሆኑን ገልጸዋል። ግድቡ የፅናት፣ የራስን መቻል እና የአህጉራዊ ኩራትና የአንድነት ብርሃን መሆኑንም ተናግረዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሕዝባቸውን በማስተባበር ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት መስጠቱንም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ገንዘባቸውን፣ እውቀታቸውን እና ጉልበታቸውን ሳይሰስቱ ለዓመታት በመትጋት እውን ያደረጉት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካ በራሷ አቅም ታላላቅ ፕሮጀክቶችን እንደምታሳካ ህያው ምስክር ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራሳቸው አቅም ማከናወን አይችሉም የሚለውን የተዛባ ትርክት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሙሉ ለሙሉ መቀልበሱንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የሕዝቧን የተደመረ አቅም በመጠቀም ብሔራዊ ፕሮጀክቷን እውን አድርጋለች ያሉት የሚዲያ ባለሙያዎቹ ፥ ግድቡ አፍሪካውያን ሲተባበሩ የጋራ ህልማቸውን እውን ማድረግ እንደሚችሉ ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካን አቅም፣ ታላቅነትና በልጆቿ ጥረት ግቧን ማሳካት እንደምትችል ህያው ማሳያ መሆኑንም አንስተዋል። ግድቡ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ጉልህ አበርክቶ ያለው መሆኑንም የሚዲያ ባለሙያዎቹ ጠቅሰዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ዋጋ ከፍለው ያሳኩት አህጉራዊ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል። ለመላው አፍሪካውያን የኩራት ምንጭ የሆነው ሕዳሴ ግድብ በአህጉሪቱ አዲስ የይቻላል የለውጥ ጉዞን ያቀጣጠለ መሆኑን ገልጸዋል። የበለጸገችና እና አንድነቷ የጠነከረ አፍሪካን እውን በማድረግ ሂደት ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ጠቁመዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የበርካታ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ መመረቁ ይታወሳል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የገበያ ማዕከላቱ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ለገበያ መረጋጋት ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው
Dec 1, 2025 61
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የተገነቡ ትላልቅ የገበያ ማዕከላት አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ መረጋጋትና ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት በመፍጠር ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑ ተገለጸ። በአዲስ አበባ ከተማ የምርት ፍላጎትና አቅርቦትን በማመጣጠን የፍጆታ ምርቶችን በአንድ ቦታ ለመሸመት አማራጭ የግብይት ማዕከላት አለመኖር ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል። የከተማ አስተዳደሩ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታትና የገበያውን ሁኔታ ለማረጋጋት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ ግዙፍ የገበያ ማዕከላት ግንባታ አንዱ ነው። በገበያ ማዕከላቱ የግብይት ሥርዓቱ ላይ የነበሩ የተንዛዙ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ ሸማቹ በተመጣጣኝ ዋጋ የሚፈልገውን ምርት እንዲያገኝ ዕድል ፈጥረዋል። በከተማዋ መግቢያ በሮች የተገነቡ የገበያ ማዕከላት የምርት አቅርቦትና ፍላጎትን በማጣጣም ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት መፍጠራቸውን ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ሸማቾች፣ ነጋዴዎችና አምራቾች ተናግረዋል።   ሸማች ሙሉነሽ ደምሴ እና ዮሴፍ በቀለ በአቅራቢያቸው የተከፈቱ የገበያ ማዕከላት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እንዳስቻሏቸው ተናግረዋል።   በተለይም የፍጆታ ዕቃዎችን በአንድ ቦታ ላይ ማግኘት መቻላቸው ጊዜና ጉልበት እንደቆጠበላቸው በማንሳት።   በገበያ ማዕከላቱ ምርቶችን የሚያቀርቡ ነጋዴዎች በበኩላቸው ቀደም ሲል የነበረው የግብይት ሰንሰለት የተንዛዛና ለህገወጥነት የተጋለጠ መሆኑን አስታውሰዋል።   በገበያ ማዕከላቱ ከአምራቹ በቀጥታ የሚመጡ ምርቶችን ሸማቹን ማህበረሰብ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ማስቻሉን የተናገሩት ደግሞ ነጋዴ አበራሽ ወልደሩፋኤል እና ሀጂ ሁሴን የሱፍ ናቸው።   ከአምራቾች መካከል ጉርሜሳ ጀልቀባ በገበያ ማዕከላቱ የግብይት እሴት ሰንሰለቱ እንዲያጥር በመደረጉ የተረጋጋ የምርቶች ዋጋ እንዲኖር አስችሏል ነው ያሉት።   የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሀቢባ ሲራጅ በበኩላቸው በከተማዋ የነበሩ አላስፈላጊ የግብይት ሰብሰለቶችን በማስወገድ በከተማዋ መግቢያ በሮች ላይ አምስት ትላልቅ የገበያ ማዕከላት መገንባታቸውን አንስተዋል። ማዕከላቱ አላስፈላጊ የንግድ ሰንሰለትን በማሳጠር አምራቹን ነጋዴውንና ሸማቹን በቀጥታ እንዲገናኙ አድርገዋል ነው ያሉት። ከዚህ ባለፈ በአራት የግብይት ቦታዎች የተጀመረው የቅዳሜና እሁድ ገበያ አሁን ላይ ወደ 219 ከፍ ማለቱ ለገበያ መረጋጋት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ መግቢያ በሮች የተገነቡት 5ቱ ዘመናዊ የገበያ ማዕከላት ላፍቶ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ቁጥር 1፣ ላፍቶ ሁለገብ ገበያ ማዕከል ቁጥር 2 (ዘመናዊ ሀይፐር ማርኬት እና ሁሉንም የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርች ወዘተ በአንድ ማዕከል ያየዘ)፣ ለሚ ኩራ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከል፣ ኮልፌ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከል፣ አቃቂ ቃሊቲ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከላት ናቸው። የገበያ ማዕከላቱ ዘመናዊ የግብይት ስርዓት እንዲኖር በማድረግ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ፍትሃዊ የግብይት ስርዓት እንዲሰፍን እያስቻሉም ይገኛሉ።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት መሰረት የሆኑ ቁልፍ ስኬቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል
Dec 1, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት መሰረት የሆኑ ቁልፍ ስኬቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉቀን ቀሬ ገለጹ። የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተተከሉ ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎችን በይፋ አገልግሎት አስጀምሯል።   የContinious Operating Reference Station /CORS/ -ጣቢያ በቋሚነት መሬት ላይ የሚተከል የሳተላይት መረጃን ያለማቋረጥ የሚቀበልና የሚያደራጅ ቴክኖሎጂ ነው ተብሏል። እንዲሁም የአንድን ቦታ መገኛ ከጂ ፒ ኤስ ሳተላይቶች 24 ሰዓት በመቀበል ከፍተኛ ጥራት ያለው መረጃ የሚያቀርብ እንደሆነም ተገልጿል። የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉቀን ቀሬ እንደገለጹት፥ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ባለፉት አምስት ዓመታት ለዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት መሰረት የሆኑ ቁልፍ ስኬቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል። የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በማስጀመረ፣ በቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ግንባታ፣ በህግ ማእቀፎች እንዲሁም በ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ በክህሎት ግንባታ ለውጥ መምጣቱን ጠቁመዋል።   ከሳተላይት መረጃ መቀበያ ጀምሮ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ሠፋፊ ተግባራት መከናወናቸውን በማንሳት፥ በቀጣይም ለዲጅታል መሠረተ ልማትና ለዲጅታል ኢኮኖሚ መስፋፋት በትብብር እንደሚሠራ ጠቁመዋል። የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን በበኩላቸው፥ ዛሬ ሥራ የጀመሩት ጣቢያዎች በከተሞች እየተመዘገበ ያለውን እመርታዊ ለውጥ በማጠናከር ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አንስተዋል።   በተለይም ከተሞችን በፕላን እንዲሁም በከተሞች ያለ መሬትን ቆጥሮ መዝግቦ በፍትሀዊነት ለመምራት እና የቅየሳን ትክክለኛነትን ለማረጋገጥ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖራቸው ጠቅሰዋል። ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በቀጣይም 14 ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎች (Continious Operating Reference Station /CORS/ ለመገንባት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ (ዶ/ር)፥ ዛሬ ሥራ የጀመሩት መረጃ ተቀባይ ጣቢያዎች ለቅየሳ ሙያተኞች፣ ለተመራማሪዎች፣ ለአደጋ ስጋት ተንታኞች፣ ለመልክዓ ምድር እና ለልዩ አገልግሎት ካርታ አዘጋጅ ባለሙያዎች የቦታዎችን አሁናዊ ሁኔታ መረጃ ለማግኘት እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።   የህንጻ፣ የመንገድ፣ የድልድይ እና ግድብ ግንባታ ፕሮጀክቶች ጥራት ባለው ጂኦስፓሻል መረጃ ላይ ተመስርተው እንዲነደፉና እንዲገነቡ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው ጠቁመዋል። የግብርና፣ የኢንዱስትሪ፣ የማዕድንና ሌሎች የኢኮኖሚ ዘርፎች እንዲዘምኑ በቂ መረጃ በማቅረብ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖራቸውም ነው ያነሱት። በተጨማሪም የመሬት አስተዳደር ዘመናዊ እና ጥራት ያለው እንዲሆን ያስችላሉ ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ ጣቢያዎቹን ለቅየሳ ስራዎች እና ለካርታ ዝግጅት እንዲሁም ምርምር ለመስራት በሰፊው እንደሚጠቀምባቸው አንስተዋል።
የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎችን አገልግሎት አስጀመረ
Dec 1, 2025 174
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተተከሉ ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎችን በይፋ አገልግሎት አስጀምሯል። የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን በዚሁ ወቅት፥ ዛሬ ሥራ የጀመሩት ጣቢያዎች በከተሞች እየተመዘገበ ያለውን እመርታዊ ለውጥ በማጠናከር ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አንስተዋል።   በተለይም ከተሞችን በፕላን እንዲሁም በከተሞች ያለ መሬትን ቆጥሮ መዝግቦ በፍትሀዊነት ለመምራት እና የቅየሳን ትክክለኛነትን ለማረጋገጥ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖራቸው ጠቁመዋል። በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ አሰጣጥን በማዳበር እና ተጠቃሚዎች በቀላሉ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላሉ ነው ያሉት። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በቀጣይም 14 ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎች (Continious Operating Reference Station /CORS/ ለመገንባት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉቀን ቀሬ በበኩላቸው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለዲጂታል ልማት መሰረት የሆኑ ቁልፍ ስኬቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን ጠቁመዋል።   የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ሠፋፊ ተግባራት መከናወናቸውን በማንሳት፥ በቀጣይም ሚኒስቴሩ ከሳተላይት መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎችን ለማስፋፋት በትብብር እንደሚሠራ ጠቁመዋል። የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ (ዶ/ር)፥ ዛሬ ሥራ የጀመሩት መረጃ ተቀባይ ጣቢያዎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተሟላላቸው ናቸው ብለዋል። ለቅየሳ ሙያተኞች፣ ለተመራማሪዎች፣ ለአደጋ ስጋት ተንታኞች፣ ለመልክዓ ምድር እና ለልዩ አገልግሎት ካርታ አዘጋጅ ባለሙያዎች የቦታዎችን አሁናዊ ሁኔታ መረጃ ለማግኘት እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።   የህንጻ፣ የመንገድ፣ የድልድይ እና ግድብ ግንባታ ፕሮጀክቶች ጥራት ባለው ጂኦስፓሻል መረጃ ላይ ተመስርተው እንዲነደፉና እንዲገነቡ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው ጠቁመዋል። የግብርና፣ የኢንዱስትሪ፣ የማዕድንና ሌሎች የኢኮኖሚ ዘርፎች እንዲዘምኑ በቂ መረጃ በማቅረብ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖራቸውም ነው ያነሱት። በተጨማሪም የመሬት አስተዳደርን ዘመናዊ እና ጥራት ያለው እንዲሆን ያስችላሉ ብለዋል። ኢንስቲቲዩቱ ይህን ጣቢያዎቹን ለቅየሳ ስራዎች እና ለካርታ ዝግጅት እንዲሁም ምርምር ለመስራት በሰፊው እንደሚጠቀምባቸው አንስተዋል። የContinious Operating Reference Station /CORS/ -ጣቢያ በቋሚነት መሬት ላይ የሚተከል የሳተላይት መረጃን ያለማቋረጥ የሚቀበልና የሚያደራጅ ቴክኖሎጂ ነው ተብሏል። እንዲሁም የአንድን ቦታ መገኛ ከጂ ፒ ኤስ ሳተላይቶች 24 ሰዓት በመቀበል ከፍተኛ ጥራት ያለው መረጃ የሚያቀርብ እንደሆነም ተገልጿል።  
የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው የዲጂታል ግብርና ኮንፍረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ይጀመራል
Dec 1, 2025 138
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው የዲጂታል ግብርና ኮንፍረንስ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል። “ኢኖቬሽን እና የዲጂታል መፍትሄዎችን ጠንካራ፣ አረንጓዴ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብርና ዘርፍ ግንባታ በመጠቀም የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ ብሩህ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የዲጂታል ግብርና ኤክስቴሽን አገልግሎት፣ የግብርና ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን፣ የገበያ ተደራሽነት፣ የእሴት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የግብርና ምርታማነትን ከአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም መገንባት ጋር ያስተሳሰረ አካሄድን መከተል፣ የግብርና ፖሊሲዎችና የህግ ማዕቀፎች ትግበራ በኮንፍረንሱ የሚመከሩባቸው አጀንዳዎች ናቸው። ኮንፍረንሱ የእውቀት ሽግግር እና ፖሊሲ ተኮር ውይይቶች የሚደረግበት ሲሆን ስኬታማ የሀገራት የግብርና ኢኒሼቲቮች ለተሳታፊዎች ይቀርቡበታል። በአፍሪካ የዲጂታል ግብርና መፍትሄዎችን ተደራሽነት የሚደግፉ ስትራቴጂዎች የመለየት እና አጋርነቶችን ማጠናከር ከሁነቱ የሚጠበቅ አበይት ውጤት መሆኑን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ 2024 ያፀደቀውን አህጉራዊ የዲጂታል ግብርና ስትራቴጂ ተፈጻሚነት የማሳደግ ጥረት አካል መሆኑንም አመልክቷል። የግብርና ስትራቴጂው ከአጀንዳ 2063 እና ከረጅም ጊዜ የአፍሪካ የልማት እቅድ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ነው ህብረቱ የገለጸው። ስትራቴጂው ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ(አይሲቲ) በመጠቀም አህጉራዊ የዲጂታል ገበያ መገንባት እና ግብርናን ከአፍሪካ የዲጂታልና ዘላቂ ልማት ግቦች ጋር የማስተሳሰር ግብ ያለው ነው። እስከ ሕዳር 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው በዚህ መድረክ የአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ፖሊሲ አውጪዎች፣ የግብርና ተመራማሪዎች እና ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች፣ አርሶ አደሮች እና የአርሶ አደር ተቋማት፣ የምርምር ተቋማት፣ባለሀብቶች፣ የልማት አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ።
የኢዜአ ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማትን አሸነፈ
Nov 30, 2025 214
አዲስ አበባ፤ሕዳር 21/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት አሸናፊ ሆኗል። ሽልማቱን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) እጅ ተረክቧል።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ ነው። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በመድረኩም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋዜጠኛ ጌትነት ሽንቁጤ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ አሸናፊ በመሆን ሽልማቱን ተቀብሏል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ የተለያዩ ሰፋፊ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል።
ስፖርት
ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ 
Dec 1, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ስምንተኛ ሳምንት መርሐግብር ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 1 ለ 0 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ብርሃኑ በቀለ በአራተኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በውድድር ዓመቱ ስድስተኛ ድሉን ያስመዘገበው ሲዳማ ቡና በ19 ነጥብ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል። በሊጉ ሁለተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በስምንት ነጥብ ከነበረበት 12 ደረጃ ወደ 14ኛ ዝቅ ብሏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው ሌላኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ሀዲያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 ረቷል።   አቡበከር አዳሙ በ11ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ ላይ አሳርፏል። በሊጉ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮጵያ ቡና በ10 ነጥብ ደረጃውን ከ15ኛ ወደ 10ኛ አሻሽሏል። በውድድር ዓመቱ ሶስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሀዲያ ሆሳዕና በሰባት ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ምድረገነት ሽሬ ሃዋሳ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ይጫወታል
Dec 1, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ስምንተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከመርሃ ግብሮቹ መካከል ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቀኑ 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው ሰባት ጨዋታዎች አምስቱን ሲያሸንፍ ሽንፈት ያስተናገደው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በቀሪው አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 11 ግቦችን ሲያስቆጥር አራት ግቦችን አስተናግዷል። ሲዳማ ቡና በ16 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዟል። የ2016 ዓ.ም የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው ሰባት ጨዋታዎች መካከል ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። አንድ ጊዜ ሲሸነፍ አምስት ጊዜ አቻ ወጥቷል። ስምንት ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ በተመሳሳይ ስምንት ግቦች ተቆጥረውበታል። ንግድ ባንክ በስምንት ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሲዳማ ቡና ካሸነፈ የሊጉን መሪነት ያጠናክራል። በአንጻሩ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድል ከቀናው ወደ አሸናፊነት መንገድ ይመለሳል። በሌላኛው መርሃ ግብር ምድረገነት ሽሬ ከሃዋሳ ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። ምድረገነት ሽሬ በውድድር ዓመቱ ባካሄዳቸው ሰባት ጨዋታዎች ሁለቱን አሸንፎ በሁለቱ ተሸንፎ ሶስት ጊዜ አቻ ተለያይቷል። ስድስት ግቦችን ሲያስቆጥር አምስት ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በዘጠኝ ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ በሊጉ ካደረጋቸው ሰባት ጨዋታዎች መካከል አራቱን በድል ሲወጣ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪው አንድ ጨዋታ ነጥብ ተጋርቷል። በሰባቱ ጨዋታዎች ላይ ዘጠኝ ግቦችን ሲያስቆጥር አምስት ጎሎች ገብተውበታል። ሃዋሳ ከተማ በ13 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ኢትዮጵያ ቡና ከሀዲያ ሆሳዕና ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው ሰባት ጨዋታዎች መካከል ሁለቱን ያሸነፈው ኢትዮጵያ ቡና አራት ጊዜ ተሸንፏል። አንድ ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥቷል። በጨዋተያዎቹ ላይ ስድስት ግቦችን ሲያስቆጥር ስምንት ግቦችን አስተናግዷል። ቡናማዎቹ በሰባት ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ሀዲያ ሆሳዕና በሊጉ እስከ ማሸነፍ የቻለው አንድ ጨዋታ ብቻ ነው። ሁለት ጊዜ ሽንፈት ሲገጥመው በቀሪ ሶስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። አምስት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ሰባት ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ ከተጋጣሚው እኩል ሰባት ነጥብ በመሰብሰብ በግብ ክፍያ ተበልጦ 16ኛ ደረጃን ይዟል።
በተጠባቂው ጨዋታ ቼልሲ እና የሊጉ መሪ አርሰናል አቻ ተለያዩ
Nov 30, 2025 137
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 21/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ13ኛ ሳምንት ጨዋታ ቼልሲ እና አርሰናል አንድ አቻ ተለያይተዋል። ማምሻውን በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ትሬቮህ ቻሎባህ በ48ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ቼልሲ መሪ ሆኗል። ሚኬል ሜሪኖ በ59ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል አርሰናል አቻ መሆን ችሏል። በጨዋታው ላይ የቼልሲው የአማካይ ተጫዋች ሞሰስ ካይሴዶ በ38ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ተሰናብቷል። ይህም በቡድኑ እንቅስቃሴ ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። አርሰናል በጨዋታው ላይ ያገኘውን የቁጥር ብልጫ በሚገባ መጠቀም አልቻለም። ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ በ24 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። የሊጉ መሪ አርሰናል ነጥቡን ወደ 30 ከፍ አድርጓል። ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ዝቅ ብሏል። ዛሬ በተደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ሊቨርፑል ዌስትሃም ዩናይትድን 2 ለ 0፣ ማንችስተር ዩናይትድ ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 አሸንፈዋል። ብራይተን ኖቲንግሃም ፎረስትን 2 ለ 0 ሲረታ አስቶንቪላ ዎልቭስን 1 ለ 0 አሸንፏል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያውያን የደመቁበት የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ
Dec 1, 2025 99
ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ ተከናውኗል። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ የሽልማት መርሃ ግብሩ የሚዲያ አጋር ሲሆን የሁለት ቀኑን የሽልማት መርሃ ግብር የቀጥታ ስርጭት ሽፋን በመስጠት ለመላው አፍሪካውያን ተደራሽ አድርጓል። የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ(አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ አድርጓል። የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያን ጎብኝተዋል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች ተከናውኗል። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ያስገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ከ94ቱ ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ሶስቱ በተለያዩ ዘርፎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ አሸናፊ በመሆን ሽልማቱን ተቀብሏል። ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ ሽልማቱን የተጎናጸፈው “Climate Intelligence for Survival: IGAD’s Push for Accurate, Actionable Data” በሚል ርዕስ በጻፈው ጽሁፍ ነው። የጋዜጠኛ ጌትነት ጽሁፍ በኢጋድ ቀጣና ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና የሚዳስስ ነው። በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰት ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋዎችና ኢ-ተገማች የአየር ጸባይ ለውጦች ዜጎችን በማፈናቀል እና በቁም እንስሳት ላይ ያደረሱትን ጉዳት ይቃኛል። ትክክለኛ፣ ጊዜውን የጠበቀና ለተግባር ምላሽ የሚያገለግሉ የአየር ንብረት መረጃዎች የማይበገር አቅም ለመገንባትና አደጋዎችን ለመከላከል ያላቸውን ሚናም ተዳሷል። በጽሁፉ ላይ የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያና ትግበራ ማዕከል(ICPAC) የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን በማጠናከር፣ የትንበያ አቅም ማሳደግና የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት የመቋቋም አቅም ላይ እያከናወነ ያለው ስራ ተቀምጧል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች፣ የአንበጣ መንጋ፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብና ሌሎች ፈተናዎችን ለመከላከል ተአማኒነት ያለው የአየር ንብረት መረጃ ወሳኝ መሆኑም ተመላክቷል። በተለይም ኑሯቸው በተለያዩ ወቅቶች ላይ ለተመረኮዙ አርሶ እና አርብቶ አደሮች መረጃው ወሳኝ መሆኑን ያስቀምጣል። ሌላኛው ተሸላሚ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (ኦቢኤ) ጋዜጠኛ ሽመክት ጉግሳ ነው። የተሸለመበት ዘርፍ በኦሮምኛ ቋንቋ በሰራው ፕሮግራም ነው። ፕሮግራሙ ዛፎች ከሰው ህይወት ጋር ያላቸውን ቁርኝት በዋናነት ይቃኛል። መንደርደሪያውን ከዓለም የዛፍ ጠቀሜታና ጥበቃ በማድረግ በኦሮሚያ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ይዳስሳል። ዛፍ መትከል ተፈጥሮና የሰው ልጅን እንዴት እንደሚጠብቅ በተቃራኒው መቁረጥ የሚያደርሰውን ጉዳትም ያስቃኛል። የ21 ደቂቃ ፕሮግራሙ የኦሮሞ ህዝብ በዘመናት መካከል ዛፎችና የደን ሀብቶች እንዲጠበቁ ያደረገው አስተዋጽኦ ተወስቶበታል። በተለይም በገዳ ስርዓት ውስጥ ዛፍን መጠበቅ ያለው ሚና በስፋት ተነስቷል። አንድ ዛፍ ለአራት ሰዎች መኖር መሠረት ይሆናል፤ ዛፍ መቁረጥ አራት ሰዎችን እንዲሞቱ ያደርጋል የሚል የአባገዳ አስተያየትም ተጠቃሽ ነው። አባ ገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ እናቶችና የአካባቢ ማህበረሰቦች ተፈጥሮን ጠብቆ በማቆየት ያላቸው ሚና ቁልፍ እንደሆነ ተመላክቷል። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መስራችና ስራ አስኪያጅ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን(ኢጋድ) የህይወት ዘመን ጋዜጠኝነት ሽልማት ተበርክቶላታል። ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በሬዲዮ ጋዜጠኝነት ግንባር ቀደምና በዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቷንም ኢጋድ ገልጿል። በብሮድካስት ሚዲያው ከ40 ዓመት በላይ የቆየችው ጋዜጠኛ መዓዛ ሸገር ኤፍኤም 102.1ን ከ18 ዓመታት በፊት በማቋቋም በኢትዮጵያ ቀዳሚ የመረጃ እና የመዝናኛ ጣቢያ እንዲሆን ማድረጓ አመልክቷል። ከጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ አበይት ፕሮግራሞች መካከል “ማንን ምን እንጠይቅልዎ?” እና “ሸገር ካፌ” ተጠቃሽ ናቸው። ጋዜጠኛዋ በፕሮግራሞቹ ህዝብን ከመንግስት አገልግሎቶች ጋር በማገናኘትና በማህበራዊ፣ የህግ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ላይ የተመረኮዙ ውይይቶች እንዲካሄዱ መድረክ መፍጠር መቻሏንም ነው የገለጸው። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መሪ ሀሳብ በሆነው የእናንተ ሬዲዮ መዓዛ በጋዜጠኝነት ሙያ ህዝብን ለማገልገልና የኢትዮጵያውያንን ድምጽ ለማጉላት ያላትን ቁርጠኝነት ኢጋድ አድንቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ኢጋድ አመልክቷል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 1, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንደገለፀው በሚቀጥሉት አሥር ቀናት ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት አካባቢዎች ላይ ቀጣይነት ይኖረዋል። ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጥቂት የደቡብ እና የደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናቶች ላይ በተዳከመ ሁኔታ ቀጣይነት ይኖራቸዋል። በዚህም የደቡብ ኦሮሚያ ዞኖች፤ የሲዳማ ክልል ዞኖች፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡባዊ ዞኖች እና የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ዞኖች በጥቂት ስፍራዎቻቸው ላይ በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚጠቁሙ ገልጿል። በሌላ በኩል ከሚኖረው የደመና ሽፋን ላይ በመነሳት በጥቂት የሰሜን፣ መካከለኛውና ደቡብ ጎንደር ዞኖች፣ ባህርዳር ዙሪያ፣ አዊ ፣ በምዕራብና ምስራቅ ጎጃም አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናት ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ትንበያው አብራርቷል። የምዕራብ ኦሮሚያ ክልል ዞኖች፣ አርሲ እና ምዕራብ አርሲ፤ ባሌ እና ምስራቅ ባሌ ዞኖች፣ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ እና የማኦኮሞ ልዩ ዞን፤ የጋምቤላ ክልል ዞኖች፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዞኖችም አልፎ አልፎ ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ። ስለሆነም በሚኖሩት ደረቅ ቀናቶች የደረሱ ሰብሎች መሰብሰብ አስፈላጊ መሆኑን ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል። በሌላ በኩል ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩም በመግለጫው ተብራርቷል። በዚህም የበጋው ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በተለይም በሰሜን፣ ምስራቅ፣ መካከለኛውና ደቡብ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የለሊትና የማለዳው ቅዝቃዜ ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየስ በታች እንደሚሆን ትንበያው ያሳያል።
የኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤን ለማስተናገድ መመረጥ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ላላት ቁርጠኝነት የተሰጠ ዕውቅና ነው
Nov 30, 2025 135
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤን ለማስተናገድ መመረጥ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ላላት ቁርጠኝነት የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል በሚደረግ ሂደት የሚዲያ ሚና ወሳኝ መሆኑንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ''ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ፤ ደኅንነቱ ለተረጋገጠ ጠንካራና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሃሳብ የ2025 የሚዲያ ሽልማት በአዲስ አበባ በማካሄድ ላይ ይገኛል።   በመድረኩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ኢጋድ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለቀጣናዊ የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስም በስትራቴጂክ ዕቅድ መምራት የሚያስችል የማስተባበር ሥራ እየሰራ አንደሚገኝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ በተግባር የተደገፈ ለውጥ አምጪ የመፍትሔ እርምጃዎች ላይ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ለጎረቤት ሀገራት ጭምር በማጋራት ውጤታማ ስራ ማከናወኗን አስረድተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአህጉሪቷ የታዳሽ ኃይል መስክ አዲስ ምዕራፍ በመክፈት የዲጂታል ሽግግር አንቀሳቃሽ ኃይል ለመሆን መብቃቱን አንስተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና ሌሎች የታዳሽ ሀይል የልማት ስኬቶች ለአፍሪካ የኢንዱስትሪና የዲጂታል ሽግግር በምሳሌነት የሚወሰዱ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የኢኮኖሚ ግንባታም 2ኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በስኬት በማስተናገድ ቀርጠኝነቷን ለዓለም ማስመስከሯን ገልጸዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላ የሚካሄደውን የመንግስታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP 32) በ2027 ለማስተናገድ በሙሉ ድምጽ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ላላት ቁርጠኝነት የተሰጠ እውቅና መሆኑን ተናግረዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመዋጋትም መገናኛ ብዙኃን ግንባር ቀደም ሚና እንዳላቸው የኢጋድ 2025 የጋዜጠኞች ዕውቅና ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ እያደገ የመጣው የመገናኛ ብዙኃን ሙያተኞች ሽልማት ቀጣናዊ ድምፆችን ለማጉላት ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። መገናኛ ብዙኃን ሙያተኞችም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ሰላምና ደኅንነትን ለማስጠበቅ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም የቀጣናውን ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሻሽል ወሳኝ የልማት እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። በብራዚል ቤለም በተካሄደው 30ኛ ጉባኤ ላይ ከሁለት ዓመታት በኋላ የሚካሄደውን 32ኛ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ (COP-32) ኢትዮጵያ እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል።
ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው
Nov 30, 2025 130
አዲስ አበባ፤ህዳር 21/2018(ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ ነው። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ያለው። በመድረኩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ፣ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ሲሆን ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ የሽልማቱ ብቸኛ የሚዲያ አጋር ነው።   በመርኃግብር በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና ይሰጣል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ከእ.አ.አ 2023 ጀምሮ እየተካሄደ የሚገኝ ዓመታዊ ሁነት ሲሆን የ2023 ሽልማት በጅቡቲ የተካሄደ ሲሆን የ2024ቱ ደግሞ በኬንያ ናይሮቢ መካሄዱም ይታወሳል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 520
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 413
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል።   ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል።   ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ለሱዳን ግጭት ዓለም አቀፍ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል- ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
Nov 19, 2025 525
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የሱዳን ግጭት ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቀናጀ ምላሽ እንዲሰጥ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ያዘጋጀው ሁለተኛ የሱዳን የልዩ ልዑኮች ፎረም ዛሬ በጅቡቲ ተካሄዷል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ተዋንያን ተሳትፈዋል። ፎረሙ በሱዳን ላለው ቀውስ የተቀናጀ መልስ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።   የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር የሱዳን ሰላም በሱዳናውያን የሚመራ፣ ቀጣናዊ ትብብር የተረጋገጠበት እና ዓለም በአንድ ድምጽ የሚደግፈው ሊሆን እንደሚገባ አመልክተዋል። በሱዳን ያለውን ግጭት ለማስቆም፣ ንጹሃን ዜጎችን ለመጠበቅ እና የኢጋድ ቀጣናን የተረጋጋ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ዋና ፀሐፊው ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን በሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደረስ፣ የሰብዓዊ እርዳታ መተላለፊያ እንዲከፈት እና ተአማኒነት ያለው የስልጣን ሽግግር እንዲኖር በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። ኢጋድ ሱዳናውያን በሀገራቸው ሰላም እና ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ክብራቸው እንዲጠበቅ ያላቸው መሻት እንዲሳካ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በመረጃው አመልክቷል።
ሐተታዎች
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 258
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል።   የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው።   ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።  
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 590
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 619
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 673
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2569
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2621
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3515
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3602
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 1826
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1208
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7026
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5514
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57384
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52365
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33060
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30575
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26576
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25289
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24876
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 24872
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57384
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52365
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33060
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30575
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ዲጂታል ግብርና፤ የአፍሪካ ግብርና አዲስ ምዕራፍ
Dec 1, 2025 83
ዲጂታል ግብርና በጥቅሉ ሲተረጎም የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ለግብርና ስራዎች መጠቀም ማለት ነው። ቴክኖሎጂዎቹ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የገበያ ተደራሽነትን በማስፋት፣ በአቅርቦት የእሴት ሰንሰለት ላይ መጠናከር፣ በቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓት፣ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀምና የአየር ንብረት ለውጥ አይገበገሬነት ስራዎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አላቸው። የዓለም የዲጂታል ግብርና ገበያ እ.አ.አ በ2022 ከ10 እስከ 12 ቢሊዮን መድረሱን የተለያዩ መረጃዎች ያመለክታሉ። እ.አ.አ በ2028 የገበያ መጠኑ ከ23 እስከ 25 ቢሊየን ዶላር እንደሚደርስ ትንበያ ተቀምጧል። የዲጂታል ግብርና በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ እና እስያ ፓሲፊክ በፍጥነት እያደገ ሲሆን በአፍሪካና ላቲን አሜሪካ ጅምር ላይ ነው ማለት ይቻላል። ሰሜን አሜሪካ 40 በመቶ እና አውሮፓ 25 በመቶ የዓለም የዲጂታል ግብርና ገበያ ድርሻን ይይዛሉ። አርሶ አደሮች ለዲጂታል ግብርና የሚያስፈልጋቸውን ቴክኖሎጂዎችን አለማግኘት፣ የዳታ ደህንነት እና የግል መረጃ ጥበቃ፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የኢንተርኔት ተደራሽነትና ባህላዊ ልማዶችን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር ማስተሳሰር ዓለም አቀፍ የዘርፉ ፈተናዎች ናቸው።   አፍሪካ ከአምስት እስከ ሰባት በመቶ(ከ500 እስከ 800 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር) የሚገመት ነው። በአፍሪካ የግብርና ቴክኖሎጂ ያለው ኢንቨስትመንት በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ዘርፉ ከ400 ሚሊየን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ፈሶበታል። በሞባይል የማማከር አገልግሎት፣ የገበያ ትስስር ማዕቀፎችና ለአርሶ አደሮች የፋይናንስ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የቴክኖሎጂዎቹ የተደራሽነትና አላምዶ የመጠቀም ውስንነት፣ የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የፖሊሲ እና የህግ ማዕቀፍ እክሎች እንዲሁ አካታችነት የአፍሪካ ፈተናዎች ናቸው። በአፍሪካ አብዛኛው ግብርና በአነስተኛ ይዞታ ባላቸው አርሶ አደሮች ላይ የተመሰረተ ሲሆን ግብርና ለአፍሪካውያን ኑሮ እና የምግብ ዋስትና ወሳኝ የሚባል ነው። በዚህ ረገድም የዲጂታል ግብርና ለግብርና ምርታማነት ማደግ፣ የአቅርቦት እጥረትን በመቅረፍና የልማት ግቦች በማሳካት ረገድ የበኩሉን ሚና ይጫወታል። ኢትዮጵያ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በጥር ወር 2017 ዓ.ም የዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ ይፋ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከግብርና ሚኒስቴር እና የጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን ፍኖተ ካርታውን በጋራ ይፋ አድርገዋል። ማዕቀፉ ከዚህ ቀደም የነበሩ የዲጂታል ግብርና ኤክስቴንሽንና ማማከር አገልግሎቶች በአንድ ጥላ ስር ያስቀመጠ ነው። ፍኖተ ካርታው የግብርና እሴት ሰንሰለቱን በሙሉ ዲጂታላይዝ የማድረግ አላማ አለው። የማማከርና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ የገበያ መረጃ፣ ዲጂታል ክህሎት፣ ሜካናይዜሽን፣ የዳታ መረጃ አሰባሰብና ዲጂታል መሰረተ ልማት የፍኖተ ካርታው አበይት ትኩረቶች ናቸው።   መንግስት ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን የዲጂታል ግብርናን ለማስፋት እየሰራ ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው የዲጂታል ግብርና ጉባኤ በአዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “ኢኖቬሽን እና የዲጂታል መፍትሄዎችን ለግብርና ዘርፍ በመጠቀም የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ ብሩህ ማድረግ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ኅብረቱ ዲጂታላይዜሽንን የልማት አጀንዳው አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የግብርናው ዘርፍም በዚህ የዲጂታላይዜሽን አህጉራዊ ስትራቴጂ ውስጥ ትኩረት እንደተሰጠው አንስተዋል። ኮሚሽኑ አባል ሀገራት ለዲጂታል ግብርና የመረጃ አጠቃቀምና አስተዳደር አመቺ ፖሊሲዎችን እንዲያዘጋጁ እና እንዲተገብሩ ድጋፍ ያደርጋል ነው ያሉት። ለአርሶ አደሮች፣ ለግብርና ባለሙያዎችና ለወጣቶች በዲጂታል ክህሎቶች ዙሪያ ሥልጠና እንደሚሰጥም አረጋግጠዋል። በአፍሪካ ዲጂታል ግብርናን እውን ለማድረግ የአባል ሀገራት መንግስታት፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች እና የምርምር ተቋማት በቅንጅት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።   የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ በበኩላቸው የአፍሪካን የግብርና ሥርዓት ለመለወጥ እና የምግብ ዋስትናን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ዲጂታል ግብርናን መተግበር የግድ ነው ብለዋል። ዲጂታል ግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የምርት ብክነትን ለመቀነስ፣ የፋይናንስና የገበያ ተደራሽነትን ለማስፋት እንዲሁም የመቋቋም አቅምን ለመገንባት ቁልፍ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ወጣቶች የአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ለኢኖቬሽንና ለዲጂታል ግብርና ትኩረት እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ለማምጣት ዲጂታል ግብርናን እንደ ቁልፍ ስልት መውሰዷንና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ዘርፉን ለማዘመን የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ በመድረኩ የተገኙት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢፋ ሙለታ(ዶ/ር) ገልጸዋል። የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን በስማርት ስልኮች አማካይነት ተደራሽ ማድረግ፣ ትክክለኛ የግብርና መረጃዎችን በአንድ ቋት መያዝና ማዘመን ላይ እየተሰራ መሆኑንና የግብርና ግብዓትን ተደራሽ ማድረግ፣ ከማሳ እስከ ገበያ ባለው ሂደት ውስጥ ያሉ የባለድርሻ አካላትን ቅንጅት ለማጎልበት ዲጂታላይዜሽን ላይ መሰራቱንም ጠቅሰዋል። የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የዲጂታል ግብርና ኤክስቴሽን አገልግሎት፣ የግብርና ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን፣ የገበያ ተደራሽነት፣ የእሴት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የግብርና ምርታማነትን ከአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም መገንባት ጋር ያስተሳሰረ አካሄድን መከተል፣ የግብርና ፖሊሲዎችና የህግ ማዕቀፎች ትግበራ የኮንፍረንሱ ተሳታፊዎች የሚመክሩባቸው አጀንዳዎች ናቸው። ኮንፍረንሱ የእውቀት ሽግግር እና ፖሊሲ ተኮር ውይይቶች የሚደረግበት ሲሆን ስኬታማ የሀገራት የግብርና ኢኒሼቲቮች ለተሳታፊዎች ይቀርቡበታል። በአፍሪካ የዲጂታል ግብርና መፍትሄዎችን ተደራሽነት የሚደግፉ ስትራቴጂዎች የመለየት እና አጋርነቶችን ማጠናከር ከሁነቱ የሚጠበቅ አበይት ውጤት መሆኑን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የኢንተርኔት ተደራሽነት በሚፈለገው መጠን አለማደግ ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ፣ የመሰረ ልማት ግንባታ እና የፖሊሲ ማዕቀፍ የዘርፉ ፈተናዎች ሲሆኑ ለአፍሪካ የዲጂታል ግብርና ትሩፋቶች ከፈተናዎቹ ይገዝፋሉ። ዲጂታል ግብርና ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ኢኮኖመሚ ልማት አንቀሳቃሽ ሞተር የመሆን አቅም አለው።
በቅሎ ወለደች
Nov 28, 2025 740
ቦንጋ፤ሕዳር 19/2017(ኢዜአ)፦ዛሬ ከወደ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ያልተለመደ ክስተት ታይቷል። ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም እንዲሉ ጉዳዩ እንዲህ ነው፤ በክልሉ ዳውሮ ዞን ዛባ ጋዞ ወረዳ ያማላ ቦካ ቀበሌ አንዲት በቅሎ ወልዳለች። መውለድ ከማይችሉ እንስሳት ተርታ የምትመደበው በቅሎ የመውለዷ ነገር አዲስ ክስተት ሆኗል። ጉዳዩን በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የበቅሎዋ ባለቤት የሆኑት አቶ ነጋሽ በተላ በተፈጠረው ነገር እጅጉን መደናገጣቸውን ገልጸዋል። በቅሎ በተፈጥሮ እንደማትወልድ የሚታወቅ ቢሆንም በቤታቸው የተከሰተውን ነገር ማመን እንደከበዳቸው ነው የተናገሩት። ከወትሮ የተለየ ነገር እንዳላሳየችና ትላንትና ማታ ባልጠበቁት ሁኔታ ወልዳ መመልከታቸውን አቶ ነጋኝ አውስተው፤ በቅሎዋ ከወለደች በኋላ ምንም አዲስ ነገር እንዳላሳየችም አስረድተዋል። በዛባ ገዞ ወረዳ የማላ ቦካ ቀበሌ የእንስሳት ባለሙያው አቶ ደረጀ ደስታ ፤ ክስተቱ ከሳይንስና ከተፈጥሮም የሚቃረን ለማመን የሚከብድ መሆኑን ገልጸዋል። የተወለደው ፍጡር የፈረስ ቅርፅ ያለው ፣ ገና ፀጉር ያላበቀለና ቀኑ ያልደረሰ እንደሆነም አስረድተዋል። ሲወለድም የሞተ ሲሆን በቅሎዋ አሁን ላይ በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሆነችና ምንም የተለየ ምልክት እንዳላሳየችም ነው ለኢዜአ የገለጹት። ይህን አዲስ ክስተት ከተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል የአቶ ነጋኝ ጎረቤት የሆኑት አቶ ባሳ ፈልታሞ፥ይህ ነገር ለማመን የሚከብድ ክስተት ነው፤ ከዚህ በፊት እንዲህ ዓይነት ነገር ሰምቼም ሆነ አይቼም አላውቅም ሲሉ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም