ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የአዲስ አበባ የልማት ስኬት መዲናዋን የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ማዕከል እያደረጋት ነው
Apr 18, 2026 4
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት መዲናዋን የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ማዕከል እያደረጋት ነው ሲሉ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ለ30ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ምልምል የፖሊስ ሠራዊት አባላት አስመርቋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ ወቅት፤ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት መዲናዋን የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ማዕከል እያደረጋት ነው ብለዋል። ለዚህም በመዲናዋ ነዋሪዎችና የፀጥታ አካላት ቅንጅት አስተማማኝ ሰላም በመኖሩ የኮንፈረንስ ቱሪዝምና የኢኮኖሚ ዕድገትን በማፋጠን ወሳኝ ሚና እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። ተመራቂ የፖሊስ አባላትም የሰላም ግንባታ ተልዕኮን በብቃት በመወጣት ህዝባቸውን በከፍተኛ ኃላፊነትና ታማኝነት ማገልገል እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ በበኩላቸው፤ ሙያዊ ክህሎት የተላበሰ እና ሙያዊ ግዳጅን በላቀ ብቃት የሚፈጽም የፖሊስ ሠራዊት ተገንብቷል ብለዋል። በተቋሙ የተወሰደው የሪፎርም እርምጃም የመዲናዋን ሰላም በማፅናት ግዙፍ የልማትና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያፋጥን ወሳኝ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። ተመራቂ የሠራዊት አባላቱም የመጪውን ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊነት በማስጠበቅ ግዳጁን በብቃት መወጣት የሚያስችል የተግባርና የንድፈ ሃሳብ ስልጠና መውሰዳቸውን ተናግረዋል። ተመራቂ የፖሊስ አባላት በበኩላቸው፤ በስልጠና ቆይታቸው ግዳጅን በብቃት መወጣት የሚያስችል የተግባርና የንድፈ ሃሳብ ዕውቀትና ክህሎት መቅሰማቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም ህዝብና መንግስት የጣለባቸውን አደራ በብቃት በመወጣት ለመጪው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊነት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ ተናግረዋል። ኮንስታብል ቢኒያም ተሾመ ሥራዬን በታማኝነት በመከወን የሕዝብ አደራ በአግባቡ ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብሏል። ኮንስታብል እንግዳየሁ አስረስ በበኩሉ፤ የአዲስ አበባ ጠቅላይ መምሪያ በሚሰጠን አቅጣጫ መሰረት ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈጸም ተዘጋጅቻለሁ ሲል ተናግሯል።
በአስተዳደሩ የሕጻናት መቀንጨርን ለማስቀረት የሥርዓተ ምግብ ሞዴል መንደሮችን በመመስረት እየተሰራ ነው
Apr 18, 2026 21
ሰቆጣ፤ ሚያዚያ10/2018 (ኢዜአ)፡-በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የሕጻናት መቀንጨርን ለማስቀረት የሥርዓተ ምግብ ሞዴል መንደሮች መመስረታቸውን የአስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የስርዓተ ምግብ ባለሙያ ወይዘሮ ወርቅ አያሌው ለኢዜአ እንደገለጹት በብሔረሰብ አስተዳደሩ የሚስተዋለውን የመቀንጨር ችግር ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ነው። መምሪያው ከሰቆጣ ቃል ኪዳን ስምምነት እና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የህብረተሰቡን የግብርና ምርታማነት በማሳደግ የተመጣጠነ ምግብ የመመገብ ባህሉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። እናቶች በጓሮ አትክልት፣ በዶሮና ፍየል እርባታ ሥራ ላይ ተሰማርተው ለልጆቻቸው የተመጣጠነ ምግብ እንዲመግቡ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ህጻናት ልጆቻቸውን በንጥረ ነገር የበለፀጉ አትክልት፣ ሥጋና ጥራጥሬ ምግቦችን በመመገብ ጤንነታቸው እንዲጠበቅና የተስተካከለ እድገት እንዲኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በእዚህም በአስተዳደሩ በሥርዓተ ምግብ ላይ የተሻለ እንቅስቃሴ ባሳዩ 69 ቀበሌዎች 82 ሞዴል መንደሮች መመስረቱን ባለሙያዋ ተናግረዋል። በእያንዳንዱ መንደር 60 የሚያጠቡ ነፍሰ ጡር እናቶችን በማሳተፍ ስርዓተ ምግብን በሚያሳድጉ የጓሮ አትክልትና የእንስሳት እርባታ ሥራዎች ላይ እንዲሰማሩ ተደርጓል ብለዋል። የመንደር ምስረታውን ወደ ሌሎች ቀበሌዎችና ወረዳዎች በማስፋት በሕፃናት ላይ የሚያጋጥመውን የመቀንጨር ችግር ሙሉ በሙሉ ለመፍታት በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አስታውቀዋል። በደሃና ወረዳ ዳብጦ ሞዴል መንደር ነዋሪ ወይዘሮ ገነት ደባሽ እንዳሉት በስርዓተ ምግብ ዙሪያ በተሰጣቸው ስልጠና መሰረት የጓሮ አትክልትና የዶሮ እርባታ ሥራ እያከናወኑ ነው። በእዚህም የጓሮ አትክልትና እንቁላልን ከተለያዩ ምግቦች ጋር በማሰባጠር ልጆቼን ለመመገብ ችያለሁ ብለዋል። በተደረገልን የጥቅል ጎመንና የቆስጣ ዘር ድጋፍ በጓሯችን የጓሮ አትክልት አልምተን ለመጠቀም ችለናል ያሉት ደግሞ በአበርገሌ ወረዳ የሳቃ መንደር ነዋሪ ወይዘሮ እሸሽ እሉ ናቸው። የጓሮ አትክልት ልማት ሥራቸው ልጆቻችውን የተመጣጠነ ምግም ለመመገብ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ የሕጻናት መቀንጨር ችግር ከሚስተዋልባቸው የተከዜ ተፋሰስ አካባቢዎች ውስጥ የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር አንዱ ነው። በሰቆጣ ቃል ኪዳን ስምምነት መሰረት መንግስት በሀገር በቀል መፍትሄ መሰረት ከሁለት ዓመት በታች የሆኑ ሕጻናት ላይ የሚደርሰውን የመቀንጨር ችግር በ2022 ዓ.ም ሙሉ ለሙሉ ለማጥፋት ግብ አስቀምጦ እየሰራ ነው። በዚህም በተከዜና ሌሎች አካባቢዎች ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ህጻናት፣ ነፍሰ ጡርና ወላድ ህጻናት ላይ የሥርአተ ምግብን ለማሻሻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየታየ መምጣቱን መረጃዎች ያሳያሉ። የሰቆጣ ቃል ኪዳን የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በማሻሻል የሕጻናትን ጤና፣ እድገትና ልማት ለማረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተም ይገኛል።
አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ከፍታ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋ ዲፕሎማት ነበሩ
Apr 18, 2026 25
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ከፍታ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋ ዲፕሎማት እንደነበሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለፁ። አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የአንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ በእንጦጦ ሐመረ ኖህ ኪዳነ ምህረት አንድነት ገዳም መካነ መቃብር ተፈፅሟል። በሥርዓተ ቀብሩ ላይ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ የሱፍ፣ የሀገራት አምባሳደሮችና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢዜአ እንዳሉት፤ አምባሳደር ቆንጅት በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ሀገራቸውን ያገለገሉ ብርቱ ዲፕሎማት ነበሩ። አምባሳደሯም በተለያዩ ሀገራት የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር በመሆን፣ በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ደግሞ በቋሚ መልዕክተኛነት ሀገራቸውን በታላቅ ኃላፊነት ማገልገላቸውን ገልጸዋል። አምባሳደር ቆንጂት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሥራ ዘመናቸውም ለበርካታ ዲፕሎማቶች በምሳሌነት የሚጠቀሱ ጠንካራና ታታሪ ዲፕሎማት እንደነበሩ አስታውሰዋል። በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ የከፍታ ጉዞም የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋና የሀገር ባለውለታ ዲፕሎማት እንደነበሩ አንስተዋል። የዲፕሎማሲ ስራ በሰዓት ሳይገደብ ሙሉ ጊዜና ትኩረት በመስጠት የሚከወን እንደሆነ ያስተማሩም ጭምር መሆናቸው ጠቅሰዋል። በጡረታ ከተገለሉ በኋላም እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ከአፍሪካ ህብረት ስራዎች በዲፕሎማሲ ዘርፉ ሲያገለግሉ መቆየታቸው ተናግረዋል። አምባሳደር ቆንጂት በህይወት በነበሩበት ወቅት በርካታ ጠንካራ ዲፕሎማቶች ያፈሩ እንደነበሩ ገልፀው፤ በቀጣይም ወጣት ዲፕሎማቶች ከሳቸው ልምድና የህይወት ተሞክሮ ተምረው በመማር ሀገራቸው ለማገልገል ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥር ነው ብለዋል። አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸውተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት ማገልገላቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በ1932 ዓ.ም በሐረር ከተማ የተወለዱት አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደር በመሆን ሀገራቸውን ለረጅም ዓመታት አገልግለዋል። አምባሳደሯም በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች በባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት፤ በአፍሪካ ሕብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በቋሚ መልዕክተኛነት ሰርተዋል። ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011 ዓ.ም ደግሞ በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ልዩ አማካሪ ነበሩ።
በክልሉ ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ፈተና ውጤታማ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ ነው
Apr 18, 2026 41
ቦንጋ፤ ሚያዚያ 9/2018 (ኢዜአ)-ተማሪዎች በ12 ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤታማ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ገለጸ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ሀላፊ ደስታ ገነሜ (ዶ/ር) በክልሉ በመደበኛ፣ በማታና በርቀት 15 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች ሀገር አቀፍ ፈተና እንደሚወስዱ ገልጸዋል። ተማሪዎቹ በሃገር አቀፍ ፈተናው ውጤታማ እንዲሆኑ በፈረቃ እንዲሁም በቅዳሜና እሁድ የማጠናከሪያ ትምህርት መሰጠቱና ማታም ጥምር ቤተመጻህፍት እንዲጠቀሙ መደረጉን አንስተዋል። በትምህርታቸው የተሻሉ ወደ 2 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች በቋሚነት ትምህርት ቤት ውስጥ አድረው እንዲያጠኑ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በሚፈለገው መጠን ተማሪዎቻቸውን ወደዩኒቨርሲቲ ላላስገቡ ትምህርት ቤቶች ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት ልዩ እገዛ እየተደረገላቸው መሆኑን አብራርተዋል። ፈተናው በበይነ መረብ የሚሰጥ በመሆኑ በትምህርት ቤቶች የኢንተርኔት መሰረተ ልማት ዝርጋታና ሌሎች ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ፈተናው ውጤታማ ለመሆን ዝግጅታቸውን ማጠናከራቸውን የገለጹት ደግሞ የቦንጋ የመሀል ከተማ እና የቢሻው ወልደዮሐንስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ተማሪዎች ናቸው። በሀገር አቀፍ ፈተናው የተሻለ ውጤት ለማምጣት ዝግጅታቸውን እያጠናከሩ እንደሆነ ከገለጹ ተማሪዎች መካከል የመሀል ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተማሪ እዮብ እምሩ እና ተማሪ ፍቅራለም አቱሞ ይገኙበታል። ትምህርት ቤቱ ከመደበኛ ትምህርት ክፍለ ግዜ በተጨማሪ የሚሰጠውን የማጠናከሪያ ትምህርት በትጋት እየተከታተሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በግልና ከጓደኞቻቸውጋር በመሆን ጠንክረው እያጠኑ መሆናቸውንና የፈተና ጥያቄዎችን በመስራት ለፈተናው እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የቢሻው ወልደዮሐንስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ተግባሩ ተስፋዬ እና ተክልዬ ተሾመ እንዳሉት፣ በውጤታቸው ተመርጠው በትምህርት ቤቱ ውስጥ አድረው እንዲያጠኑ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ እድል ፈጥሯል ። በትምህርት ቤቱ የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርትና በግላቸው የሚያደርጉት ዝግጅት በሀገር አቀፍ ፈተና ጥሩ ውጤት ለማምጣት እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል። ከማጠናከሪያ ትምህርት ባለፈ ፈተናው በበይነ መረብ ለመውሰድም የቴክኖሎጂ ድጋፍና የስነ ልቦና ዝግጅት እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በትምህርት ቤቱ የባዮሎጂ ትምህርት መምህር ቆጭቶ ገብረማሪያም ተፈታኝ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በማጠናከሪያ ትምህርት ከሚደረገው ድጋፍ ባለፈ በስነልቦናም የማብቃት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የቢሻው ወልደዮሐንስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ መምህር ጌታቸው መኮንን በበኩላቸው በትምህርት ቤቱ በአዳሪና በመደበኛ 336 ተፈታኝ ተማሪዎች እንዳሉ ጠቅሰው፣ ተማሪዎቹን ለሀገር አቀፍ ፈተና ለማብቃት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ከመደበኛው ትምህርት በተጨማሪ በተቃራኒ ፈረቃና በቅዳሜና እሁድ የማጠናከሪያ ትምህርት እንደሚሰጥና በሞዴል ፈተናዎች የማለማመድ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክትል ርዕሰ መምህሩ አክለውም እንደገለጹት ተማሪዎችን በቴክኖሎጂ ብቁ ማድረግ የሚያስችል ድጋፍና በስነ ልቦናም የማዘጋጀት ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከወራጅ ቀጠና የወጣበት ወሳኝ ድል አስመዘገበ
Apr 18, 2026 46
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ነፃነት ገብረመድህን በ38ኛው እና ፍሬው ሰለሞን በ93ኛው ደቂቃ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ32 ነጥብ ደረጃውን ከ18ኛ ወደ 14ኛ ከፍ በማድረግ ከወራጅ ቀጠና ወጥቷል። በሊጉ ሰባተኛ ድሉንም አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ34 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። ዛሬ ቀን ላይ በተካሄደ የ28ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ መቀሌ 70 እንደርታ ፋሲል ከነማን 3 ለ 0 አሸንፏል።
ፖለቲካ
የአዲስ አበባ የልማት ስኬት መዲናዋን የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ማዕከል እያደረጋት ነው
Apr 18, 2026 4
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት መዲናዋን የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ማዕከል እያደረጋት ነው ሲሉ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ለ30ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ምልምል የፖሊስ ሠራዊት አባላት አስመርቋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ ወቅት፤ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት መዲናዋን የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ማዕከል እያደረጋት ነው ብለዋል። ለዚህም በመዲናዋ ነዋሪዎችና የፀጥታ አካላት ቅንጅት አስተማማኝ ሰላም በመኖሩ የኮንፈረንስ ቱሪዝምና የኢኮኖሚ ዕድገትን በማፋጠን ወሳኝ ሚና እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። ተመራቂ የፖሊስ አባላትም የሰላም ግንባታ ተልዕኮን በብቃት በመወጣት ህዝባቸውን በከፍተኛ ኃላፊነትና ታማኝነት ማገልገል እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ በበኩላቸው፤ ሙያዊ ክህሎት የተላበሰ እና ሙያዊ ግዳጅን በላቀ ብቃት የሚፈጽም የፖሊስ ሠራዊት ተገንብቷል ብለዋል። በተቋሙ የተወሰደው የሪፎርም እርምጃም የመዲናዋን ሰላም በማፅናት ግዙፍ የልማትና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያፋጥን ወሳኝ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። ተመራቂ የሠራዊት አባላቱም የመጪውን ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊነት በማስጠበቅ ግዳጁን በብቃት መወጣት የሚያስችል የተግባርና የንድፈ ሃሳብ ስልጠና መውሰዳቸውን ተናግረዋል። ተመራቂ የፖሊስ አባላት በበኩላቸው፤ በስልጠና ቆይታቸው ግዳጅን በብቃት መወጣት የሚያስችል የተግባርና የንድፈ ሃሳብ ዕውቀትና ክህሎት መቅሰማቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም ህዝብና መንግስት የጣለባቸውን አደራ በብቃት በመወጣት ለመጪው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊነት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ ተናግረዋል። ኮንስታብል ቢኒያም ተሾመ ሥራዬን በታማኝነት በመከወን የሕዝብ አደራ በአግባቡ ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብሏል። ኮንስታብል እንግዳየሁ አስረስ በበኩሉ፤ የአዲስ አበባ ጠቅላይ መምሪያ በሚሰጠን አቅጣጫ መሰረት ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈጸም ተዘጋጅቻለሁ ሲል ተናግሯል።
የሽብርና ፅንፈኛ ኃይሎችን ተልዕኮ ለማስፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 138 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ዋሉ
Apr 18, 2026 217
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የሽብርና ፅንፈኛ ኃይሎችን ተልዕኮ ለማስፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 138 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳመለከተው ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት ፍላጎታቸውን በኃይል ለማስፈፀም ታጥቀው በጫካ ከሚንቀሳቀሱ የሽብርና ፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር የሀገሪቱን ሰላምና ደኅንነት ለማወክ እንዲሁም መጪውን ሀገራዊ ምርጫ ለማደናቀፍ ስምሪት ወስደው ሲንቀሳቀሱ ነው። በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የጥፋት ስምሪት ወስደው ሲንቀሳቀሱ በነበሩት ተጠርጣሪዎች ላይ በጥብቅ ዲሲፕሊን የመረጃ ክትትል ሲደረግባቸው ቆይቶ ከፌደራልና ክልል ፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ከሚያዚያ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተሠራ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር ውለዋል። ተጠርጣሪዎቹ አዲስ አበባን ጨምሮ በሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች እንዲሁም በተመረጡ አካባቢዎች ሽብር እና አመፅ በመቀስቀስ፤ ለታጠቁ ቡድኖች ሴሎችን በማደራጀት፤ መረጃዎችን በመስጠት፤ ጥቃትና እገታ ላይ በመሰማራት ተልዕኮ ወስደው ሲፈፅሙ የነበሩ መሆናቸው በመግለጫው ተብራርቷል። ለሽብርና ፅንፈኛ ቡድኖች ገንዘብ፣ ስንቅ፣ ወታደራዊ አልባሳት፣ መገናኛ ሬዲዮዎች፣ የስልክ ቀፎዎችንና ሲም ካርዶችን፣ ጦር መሣሪያና ተተኳሾችን በአጠቃላይ ሎጀስቲክስ ሲያሰባስቡና ሲያቀርቡ እንደነበር እንዲሁም በተመረጡ ከተሞችና ቀበሌዎች የምርጫ እንቅስቃሴዎችን ለማደናቀፍ፣ ብሔርና ሃይማኖት ተኮር ግጭቶችን ጭምር ለመቀስቀስ ስምሪት የወሰዱ ስለመሆናቸውም መረጋገጡም ተመላክቷል። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል የተወሰኑት አልሸባብና አይ ኤስ ከተባሉት ዓለም-አቀፍ አሸባሪዎች ጋር ትስስር በመፍጠር በሶማሊያ የሽብር ስልጠና የወሰዱ መሆናቸውም በመረጃ ስምሪት ተረጋግጧል፡፡ በሀገራችን አንዳንድ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ ለቡድኖቹ ሴሎችን በመመልመል ለሽብር ተግባር ሁኔታዎችን ሲያመቻቹ የነበሩ መሆናቸውም በመግለጫው ተጠቅሷል። በተጨማሪም በኦፕሬሽኑ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ተጠርጣሪዎች መካከል በሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር ላይ በመሰማራት ለሽብርና ለፅንፈኛ ቡድኖች ትጥቅና ተተኳሽ በማቅረብ የሀገራችን የፀጥታ ሁኔታ ለማባባስ ጥረት ሲያደርጉ የነበሩ ናቸው። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና የኮትሮባንድ ንግድ ላይ በመሰማራት የኢኮኖሚ አሻጥር በመፍጠር በመሰረታዊ የፍጆታ ምርት አቅርቦት ላይ እጥረት እንዲፈጠር ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸውም ተረጋግጧል። ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር በዋሉበት ወቅት ለሽብር እና ለፅንፈኛ ቡድኖች ሊተላለፉ በዝግጅት ላይ የነበሩ የተለያዩ የጦር መሣሪያዎች፣ ተቀጣጣይ ፈንጂዎችና ቦንቦች፣ ተተኳሾች፣ የተለያዩ የውጭ ሀገር የገንዘብ ኖቶች እንዲሁም የኮንትሮባንድ እቃዎች አብረው እንደተያዙ በመግለጫው ተጠቅሷል። በተጠቀሱት ዝርዝር የሽብር እንቅስቃሴዎች ጨምሮ በተለያዩ የጥፋት ድርጊቶች ላይ ተሰማርተው የነበሩ በድምሩ 138 ተጠርጣሪዎች ከሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና ከክልል ፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በሕግ ቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉ ተመላክቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የሽብር እና የጥፋት ቡድኖችን ድብቅ ፍላጎት ለማክሸፍና የግንኙነት መረባቸውን ለመበጣጠስ ተጨማሪ ክትትሎችን እና ጥናቶችን እያደረገ እንደሆነ፤ በተለይም መጪው ሀገራዊ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲካሄድ አስፈላጊውን ቅድመ-ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጿል፡፡ ኅብረተሰቡም ይህን በመረዳት የተለመደውን ቀና ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ መሰል የጥፋት ድርጊቶችን በመጠቆም ከአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ እና ከመላው የሀገራችን የፀጥታ ኃይሎች ጎን እንዲቆም ጥሪውን አቅርቧል።
ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ ይሰራል የምንለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
Apr 18, 2026 163
ወልቂጤ፤ ሚያዚያ10/2018 (ኢዜአ):-ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ ይሰራል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ማራዘሙ ይታወቃል። ይህም በተለያየ ምክንያት የመራጭነት ካርድ ያልወሰዱ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ ዕድል ያመቻቸ ነው። የጉራጌ ዞን ነዋሪዎችም ለመራጭነት የሚያበቃቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ለሃገር ዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ ቅድሚያ ሰጥቶ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ነው የተናገሩት። በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ጋህራድ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አብዱ ሽኩር ይወክለኛል ለሃገር ሰላምና ልማት ይሰራል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ለመራጭነት እድሜው የደረሰ ዜጋ የመራጭነት ካርድ ሊያወጣ እንደሚገባ የመከሩት አርሶ አደር አብዱ፣ በድምጻቸው ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫውን እለት እየተጠባበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የወልቂጤ ከተማ ነዋሪው ወጣት አቤል ባንቀስራ በበኩሉ፣ ዴሞክራሲያዊ መብቱን በመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዱን ገልፆ፤ ሌሎችም የሱን አርአያነት በመከተል የምርጫ ካርድ እንዲወስዱ ከልምዱ መክረ ሀሳብ መስጠቱን ጠቁሟል ። በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ልዩ ድጋፍ ለሚሹ አካል ጉዳተኞች የተሻለ ፖሊሲና አቅጣጫ ያላቸውን የፖለቲካ ፓርቲዎች እየተከታተለ መቆየቱንም አመላክቷል ። "ምርጫ የዜጎችን ተሳትፎና ፍቃድ በማግኘት በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመንግስት ስልጣን የሚያዝበት ስርዓት በመሆኑ ይበጀናል ያልነውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል" ያሉት ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ጋሻው መክብብ ናቸው ። ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ምርጫ ጠንካራና ለሁሉም የምትሆን አገር ለመገንባት መሰረት በመሆኑ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ የዜግነት ግዴታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በቀሪ ቀናትም የምርጫ ካርድ ያላወጣ ነዋሪ በምርጫ ጣቢያዎች ተመዝግቦ ካርዱን በእጁ መያዝ እንዳለበት መክረዋል። ለጠቅላላ ምርጫው እየተካሄደ ያለው የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም መራዘሙ በርካታ ዜጎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በመውሰድ የዕድሉ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 18, 2026 194
ከሚያዝያ 5 እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ በንፋስ ኃይል አማካኝነት ጨለማን ለመግፈፍ፣ ዐቅምን በለየ የቅድመ ጥናት እና ልዩ ዕቅድ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ዕውን አድርጋለች ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት 100 ሜጋ ዋት ንጹህ የኃይል አቅርቦት በመጨመር ወደ ዘርፈ-ብዙ እና ቀጣይነት ባለው የኃይል መጻዒ ዕጣ ፈንታ ለመገንባት የምናደርገውን ጉዞ ያጠናክረዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ አብነት ነው ብለዋል በወቅቱ። በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል፤ ከምንጊዜውም በላይ ታላቅ የምንሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉም አመላክተዋል። • ከኮፕ32 አስተናጋጅነት ጋር በተያያዘ ምክክር መደረጉ የኮፕ32 አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ መጀመሯን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል ሲሉ ገልጸዋል። ከግምገማ ባሻገር የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልኅቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው ብለዋል። • የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከዚያም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይትም፤ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በቅኝ ያልተገዙ፣ ለአኅጉሩ ነፃነትና አንድነት ድምፅ በመሆን ከጋራ የጽናት ታሪክ የሚመነጭ ጥልቅና ዘመናትን የተሻገረ ግንኙነት አላቸው ያሉት ጠላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም እንደ ሁሌው ኢትዮጵያ ከሰፊ ገበታዋ ያላትን ታላቅ ዐቅምና ዘላቂ ወዳጅነት አብረዋት ለሚጓዙ ሁሉ ለማካፈል ዝግጁ ናት ብለዋል። ጉብኝቱም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን የቆየ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለማስፋት ወሳኝ ምዕራፍን ከፍቷል ሲሉ ገልጸዋል። ከሁለትዮሽ ስብሰባው በመቀጠልም በሁለቱ ሀገራት በኩል ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጉዞ ያካበተችውን ልምድ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማካፈል እንዲሁም ከአጋሮቻችን የተለያዩ ዕይታዎችን በመቅሰም ለአኅጉሩ ዕድገት ዘላቂና አፍሪካዊ መፍትሔዎችን በጋራ ለማፍለቅ እንደ ወሳኝ መሠረት ያገለግላሉ ነው ያሉት። • የፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ባሳለፍነው ሳምንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ቀጣይ ትብብሮችን በምናጠናክርባቸው ቁልፍ መስኮች ላይ መክረናል ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም፤ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ፣ የተሻገረ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ በበቂ ሁኔታ ዜጎችን ሥራ ለማስያዝ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሚና አይተኬ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሥራ ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚ ያሸጋግራል፣ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሻገር እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ያገለግላል በማለት አብራርተዋል። በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነት አንዱ አንጓ ነው በማለት አስረድተዋል። የብዙ መንግሥታትና የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል። አክለውም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል። አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል። እንዲሁም የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግሥት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አብራርተዋል። ከተማ አያስፈልግኝም፤ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አመላክተዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በወሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገራችን በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ሥር እየሰደደ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሐሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል። እንዲሁም በ "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ሥራ ማስጀመራቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ማሳያ እና የወሎ የብልጽግና ተስፋ ነው ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የ"መደመር" ዕሳቤ በተግባር የታየበት፣ የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለ ሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት ነው ሲሉም ገልጸል። ያየነው ልማት የሰላም ውጤት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ በማለት፤ በአንድነት እና በትጋት ከሠራን ይህ ቀጣና የዕድገትና ብልጽግና መዳረሻ መሆኑ አይቀሬ ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንትን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት መሠረተ-ልማት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ግብዓቶችን በማመላለስ የኢኮኖሚያችን የደም ሥር፣ የብልጽግናችን መሠረት ነው ብለዋል። በዐውደ ርዕዩ የተመለከትነውም ወሳኝ የልማት ተቋሞቻችን፣ መሠረተ-ልማትን እንደ ሀገር በቅንጅትና በትብብር የመምራት አዲስ የሥራ ባህል እየገነቡ መሆናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግሥት በመንገድ፣ በኃይል፣ በመስኖ፣ በባቡርና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፍ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚሠራውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። አሁን ያለንበት ወቅት የሥራ፣ የውጤት እና የተስፋ ዘመን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ትናንት የተገነባው ለዛሬ፣ ዛሬ የምንገነባው ደግሞ ለነገው ትውልድ ኩራት እና የብልጽግና ዋስትና ነው ብለዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መሳተፍ የሚያስችለንን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል- የመዲናዋ ነዋሪዎች
Apr 18, 2026 215
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ የምርጫ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በወቅቱ በመውሰድ በምርጫው በንቃት ለመሳተፍ ዕለቱን እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ሲያካሂድ ቆይቷል። በተጨማሪም ቦርዱ የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሟል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥበት ዕለት ነው፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ድምጻቸውን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካካል አቶ ጃፋር መሐመድ እንዳሉት፤ ምርጫ ለአንድ ሀገር ዜጎች በፈቀዱትና በመረጡት መንገድ የስልጣን ሽግግር እንዲኖር በማድረግ የጋራ ዕጣ ፋንታን በጋራ የሚወስኑበት ትልቅ እድል ነው። በመሆኑን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸው፤ ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ በሽር ኢማም በበኩላቸው በሌሎች ሐሳብና ፍላጎት ስር ላለመውደቅ የምርጫ ካርድ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን ጠቅሰው፤ የመመዝገቢያው ጊዜ አልፎ ከመቆጨት ከመጸጸትን በወቅቱ መጠቀም እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። በዚህም የራስንና ቀጣይ የአገርን ሰላምና ኢኮኖሚያዊ እደገት ብሎም የዜጎችን ዘላቂ ተጠቃሚነት ማረጋጋጥ ይቻላል ብለዋል። አንድ ሀገር ልትመራ የምትችለው የራሷ መሪ ሲኖራት ነው መሪዋን ደግሞ የሚመረጠው በህዝቦቿ ነው በመሆኑም የአገሬን መሪ መምረጥ ውዴታ ብቻ ሳይሆን ግዴታዬም ጭምር ያለችን ወይንሸት ፊፋ ናት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሲያከናውን የነበረው የመራጮች ምዝገባ ማራዘሙ በተለያዩ ምክንያቶች ተመዝግበው ካርድ ለማውጣት ያልተመቻቸው ዜጎች ትልቅ እድል ነው ብላለች። ምርጫ የወደፊት ህልሜን ያሳካልኛል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ የሚረዳኝ አጋጣሚ በመሆኑ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለው ያለን ደግሞ ወጣት መሐመድ ዘይኔ ነው።
ወጣቶች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በመውሰድ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል
Apr 18, 2026 179
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በቀሪ ቀናት በመውሰድ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የክልሎች የወጣቶች ቢሮ ሀላፊዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል። ቦርዱ ለአንድ ወር የሚቆየውን የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሞታል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥበት ዕለት ነው፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። ከክልሎች የተወጣጡ የወጣቶች ቢሮ ሀላፊዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ምርጫ በሀገር ጉዳይ የመወሰን እድል ስለሆነ ወጣቶች ይህን ተረድተው በቀሪ ቀናት ካርድ መውሰድ ይኖርባቸዋል። ምርጫ ለሀገር እድገት እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እጅግ ወሳኝ መሆኑንም ነው የተናገሩት። ዜጎች በየጊዜው በምርጫ አማካኝነት መሪዎቻቸውን በመምረጥ፤ ይህም ይጠቅመናል ሀገርን ወደ ተሻለ ደረጃ ያደርሳል ለሚሉት እጩ የመንግስትን ስልጣን በህጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ በአደራ የሚሰጡበት ነው። በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ በሚገኘው የመራጮች ምዝገባ በመሳተፍ ካርድ ያልወሰዱ ወጣቶች ተመዝግበው ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ነው የጠየቁት። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ሱልጣን አሊ እንደገለጸው፤ በክልሉ ወጣቶች በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ በምርጫ ሂደቱ ላይ እንዲሳተፉ የማንቃት ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብሏል። ምርጫው በሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ሂደት እንዲጠናቀቅ ወጣቶች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ በንቃት በባለቤትነት ስሜት መሳተፍ አለባቸው ሲልም ገልጿል። በሲዳማ ክልል የወጣቶች ማህበር አባል በቃሉ መሰረት በበኩሉ፤ የወጣቶችን ተሳትፎ ለማጎልበት ከምርጫ ምዝገባ ጀምሮ ተሳታፊ እንዲሆኑ ከሲቪክ ማህበራትና ሌሎች አጋሮች ጋር እየተሰራ ነው። ምርጫ በሀገር ጉዳይ ላይ የመሳተፍ ብቻ ሳይሆን፤ የመወሰንም እድል በመሆኑ ወጣቶች ከምዝገባ ጀምሮ በንቃት ሊሳተፉ ነው ሲልም ተናግሯል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮሚሽነር ወጣት ማርቆስ ማቲዎስ፤ ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመራጭነት፣ በታዛቢነት በእጩ ተወዳዳሪነት እንዲሳተፉ በተከናወኑ ስራዎች ውጤቶች መገኘታቸውን ነው የገለጸው። በክልሉ ወጣቶች ከመራጭነት ባለፈ በታዛቢነትና በእጩ ተወዳዳሪነት ተሳትፎ እያደረጉ መምጣታቸውን ተናግሯል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስከ ሚያዝያ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 46 ሚሊዮን 736 ሺህ 895 ዜጎች ለመራጭነት መመዝገባቸውን አስታውቋል።
ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጭና ፕሮግራማቸውን የሚያስተዋውቁባቸው መድረኮች መመቻቸት የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመወሰን ያስችላል
Apr 18, 2026 232
ሚዛን አማን፣ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ) -የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጭና ፕሮግራማቸውን የሚያስተዋውቁባቸው መድረኮች መመቻቸት የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመወሰን እንደሚያስችላቸው የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። አስተያየት ሰጪዎቹ በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን ተመዝግበው የምርጫ ካርድ ያልወሰዱ ዜጎች በቀሪ ጥቂት ቀናት በመመዝገብ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን መጠቀም እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ የተለያዩ የጊዜ ሰሌዳዎችን አውጥቶ ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል። ከዚህ ውስጥም ለመራጭነት የሚያበቃ የምርጫ ካርድ መውሰጃ ጊዜ ሰሌዳ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናቶች ቀርተውታል ። የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ለሀገር የሚጠቅም ፓርቲን ለይቶ ድምጻቸውን ለመስጠት ፓርቲዎች የሚያደርጓቸውን ክርክርች እና ያሏቸውን ፕሮግራሞቻቸውን በመከታተል ላይ ናቸው። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ማለቶ ታከለ እንደሚሉት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን የፐሊሲ አማራጮችን በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን በመከታተል በምርጫው ንቁ ተሳታፊ ለመሆን ዝግጅት እያደረጉ ነው ። በፌዴራል ደረጃ በቴሌቪዥን ከሚደረግ የምርጫ ማኒፌስቶ ማስተዋወቅ መርሐ ግብር ባሻገር በክልል ደረጃም መሰል ትግባራት መከናወናቸው ለመራጩ ሕዝብ በቂ ግንዛቤ እየተፈጠረለት መሆኑንም ጠቅሰዋል። ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በራስ ፍላጎት የሚያስተዳድረንን መንግስት የምንመርጥበት በመሆኑ እስካሁን የመራጭነት ካርድ ሳይወስዱ የዘገዩ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም በቀሪ ጊዜያት ካርድ ማውጣት ይገባቸዋል ሲሉም መክረዋል። ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ መምህርት አልማዝ ዓለምገና፤ በመገናኛ ብዙሃን የሚካሔዱ የፓርቲዎች ክርክሮችና የፕሮግራም ማስተዋወቂ መድረኮች በምርጫው ለሀገርና ለህዝብ ጠቃሚ ሀሳብ ያለውን የተሻለ ፓርቲን ወደ ስልጣን ለማምጣት ግንዛቤ እየፈጠሩላቸው መሆኑን ገልጸዋል ነገ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማየት አንድ ድምጽ ወሳኝ በመሆኑ በዴሞክራሲ ግንባታ፣ በልማትና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በማኅበራዊ አገልግሎቶች የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ በነጻነት ለመምረጥ ተዘጋጅቺያለሁ ሲሉ ገልጸዋል። ወቅቱ በሀገርና በፖለቲካ እሳቤዎች ላይ የሕዝብ ንቃተ ሕሊና የጨመረበት በመሆኑ ሰላማዊ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት ይኖራል ብለው እንደሚጠብቁ ነው የተናገሩት። ለአካባቢያችን ለውጥና ዕድገት ብሎም ለሀገር አንድነት መጠናከር የሚሰራ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የተናገሩት ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫው የሚሳተፉት ወጣት ታምራት አድማሱ እና አሻግሬ መቹል ናቸው። ለመምረጥ ከመዘጋጀት ባሻገር ለምርጫው ሰላማዊነትና መረጋጋት እንደ ወጣት ባለንበት አካባቢ ሚናችንን እንወጣለን ሲሉም አክለዋል።
ለሀገርና ለሕዝብ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - አርሶ አደሮች
Apr 17, 2026 1850
ደሴ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ለሀገርና ለሕዝብ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በደቡብ ወሎ ዞን የተሁለደሬ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዘንድሮው ዓመት ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ በማውጣት የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ነው። ከዚህ ውስጥም የእጩዎች ምዝገባ የተጠናቀቀ ሲሆን የመራጭነት ምዝገባ ሂደት ደግሞ እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ/ም እንደሚካሔድም መገለጹ ይታወሳል፡፡ የወረዳው አርሶ አደሮች እንደሚሉት የምርጫ ካርድ በማውጣት በመጪው ምርጫ ላይ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት አድርገዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት ውስጥ አርሶ አደር ሰይድ ፈንታ፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ እና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። ይወክለኛል ያልኩትን ፓርቲ ወደ ስልጣን በማምጣት ሀገሪቷን እንዲመራ በካርዴ ለመወሰን እየተጠባበኩ እገኛለሁ ብለዋል። ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅም ከፀጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ነው የሚናገሩት። አርሶ አደር መሀመድ አደም በበኩላቸው፣ በምርጫው የሚጠበቀውን ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ነው የሚናገሩት። በምርጫው ቀን ይጠቅመናል፣ ይበጀናል ለምንለው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠትና የዜግነት ግዴታችንን ለመወጣት እየተጠባበቅን እንገኛለን ሲሉም ተናግረዋል። ህገ-መንግስቱ ያጎናጸፈንን መብት ከመጠቀም ባለፈ ዴሞክራሲያዊ ልምምዱ በተሻለ መንገድ እንዲከወንና ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን የድርሻችንን እንወጣለን ነው ያሉት። የመራጭነት ካርድ መውሰድ ለምንፈልገው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠት ቁልፍ ተግባር ነው ያሉት ደግሞ አርሶ አደር ሉባባ መሀመድ ሲሆኑ ካርድ ያልወሰዱ ዜጎችም በቀሪ ጊዜያት ተመዝግበው ቢዘጋጁ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። በምርጫው ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
ፖለቲካ
የአዲስ አበባ የልማት ስኬት መዲናዋን የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ማዕከል እያደረጋት ነው
Apr 18, 2026 4
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት መዲናዋን የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ማዕከል እያደረጋት ነው ሲሉ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ለ30ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ምልምል የፖሊስ ሠራዊት አባላት አስመርቋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ ወቅት፤ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት መዲናዋን የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ማዕከል እያደረጋት ነው ብለዋል። ለዚህም በመዲናዋ ነዋሪዎችና የፀጥታ አካላት ቅንጅት አስተማማኝ ሰላም በመኖሩ የኮንፈረንስ ቱሪዝምና የኢኮኖሚ ዕድገትን በማፋጠን ወሳኝ ሚና እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። ተመራቂ የፖሊስ አባላትም የሰላም ግንባታ ተልዕኮን በብቃት በመወጣት ህዝባቸውን በከፍተኛ ኃላፊነትና ታማኝነት ማገልገል እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ በበኩላቸው፤ ሙያዊ ክህሎት የተላበሰ እና ሙያዊ ግዳጅን በላቀ ብቃት የሚፈጽም የፖሊስ ሠራዊት ተገንብቷል ብለዋል። በተቋሙ የተወሰደው የሪፎርም እርምጃም የመዲናዋን ሰላም በማፅናት ግዙፍ የልማትና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያፋጥን ወሳኝ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። ተመራቂ የሠራዊት አባላቱም የመጪውን ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊነት በማስጠበቅ ግዳጁን በብቃት መወጣት የሚያስችል የተግባርና የንድፈ ሃሳብ ስልጠና መውሰዳቸውን ተናግረዋል። ተመራቂ የፖሊስ አባላት በበኩላቸው፤ በስልጠና ቆይታቸው ግዳጅን በብቃት መወጣት የሚያስችል የተግባርና የንድፈ ሃሳብ ዕውቀትና ክህሎት መቅሰማቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም ህዝብና መንግስት የጣለባቸውን አደራ በብቃት በመወጣት ለመጪው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊነት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ ተናግረዋል። ኮንስታብል ቢኒያም ተሾመ ሥራዬን በታማኝነት በመከወን የሕዝብ አደራ በአግባቡ ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብሏል። ኮንስታብል እንግዳየሁ አስረስ በበኩሉ፤ የአዲስ አበባ ጠቅላይ መምሪያ በሚሰጠን አቅጣጫ መሰረት ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈጸም ተዘጋጅቻለሁ ሲል ተናግሯል።
የሽብርና ፅንፈኛ ኃይሎችን ተልዕኮ ለማስፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 138 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ዋሉ
Apr 18, 2026 217
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የሽብርና ፅንፈኛ ኃይሎችን ተልዕኮ ለማስፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 138 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳመለከተው ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት ፍላጎታቸውን በኃይል ለማስፈፀም ታጥቀው በጫካ ከሚንቀሳቀሱ የሽብርና ፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር የሀገሪቱን ሰላምና ደኅንነት ለማወክ እንዲሁም መጪውን ሀገራዊ ምርጫ ለማደናቀፍ ስምሪት ወስደው ሲንቀሳቀሱ ነው። በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የጥፋት ስምሪት ወስደው ሲንቀሳቀሱ በነበሩት ተጠርጣሪዎች ላይ በጥብቅ ዲሲፕሊን የመረጃ ክትትል ሲደረግባቸው ቆይቶ ከፌደራልና ክልል ፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ከሚያዚያ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተሠራ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር ውለዋል። ተጠርጣሪዎቹ አዲስ አበባን ጨምሮ በሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች እንዲሁም በተመረጡ አካባቢዎች ሽብር እና አመፅ በመቀስቀስ፤ ለታጠቁ ቡድኖች ሴሎችን በማደራጀት፤ መረጃዎችን በመስጠት፤ ጥቃትና እገታ ላይ በመሰማራት ተልዕኮ ወስደው ሲፈፅሙ የነበሩ መሆናቸው በመግለጫው ተብራርቷል። ለሽብርና ፅንፈኛ ቡድኖች ገንዘብ፣ ስንቅ፣ ወታደራዊ አልባሳት፣ መገናኛ ሬዲዮዎች፣ የስልክ ቀፎዎችንና ሲም ካርዶችን፣ ጦር መሣሪያና ተተኳሾችን በአጠቃላይ ሎጀስቲክስ ሲያሰባስቡና ሲያቀርቡ እንደነበር እንዲሁም በተመረጡ ከተሞችና ቀበሌዎች የምርጫ እንቅስቃሴዎችን ለማደናቀፍ፣ ብሔርና ሃይማኖት ተኮር ግጭቶችን ጭምር ለመቀስቀስ ስምሪት የወሰዱ ስለመሆናቸውም መረጋገጡም ተመላክቷል። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል የተወሰኑት አልሸባብና አይ ኤስ ከተባሉት ዓለም-አቀፍ አሸባሪዎች ጋር ትስስር በመፍጠር በሶማሊያ የሽብር ስልጠና የወሰዱ መሆናቸውም በመረጃ ስምሪት ተረጋግጧል፡፡ በሀገራችን አንዳንድ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ ለቡድኖቹ ሴሎችን በመመልመል ለሽብር ተግባር ሁኔታዎችን ሲያመቻቹ የነበሩ መሆናቸውም በመግለጫው ተጠቅሷል። በተጨማሪም በኦፕሬሽኑ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ተጠርጣሪዎች መካከል በሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር ላይ በመሰማራት ለሽብርና ለፅንፈኛ ቡድኖች ትጥቅና ተተኳሽ በማቅረብ የሀገራችን የፀጥታ ሁኔታ ለማባባስ ጥረት ሲያደርጉ የነበሩ ናቸው። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና የኮትሮባንድ ንግድ ላይ በመሰማራት የኢኮኖሚ አሻጥር በመፍጠር በመሰረታዊ የፍጆታ ምርት አቅርቦት ላይ እጥረት እንዲፈጠር ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸውም ተረጋግጧል። ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር በዋሉበት ወቅት ለሽብር እና ለፅንፈኛ ቡድኖች ሊተላለፉ በዝግጅት ላይ የነበሩ የተለያዩ የጦር መሣሪያዎች፣ ተቀጣጣይ ፈንጂዎችና ቦንቦች፣ ተተኳሾች፣ የተለያዩ የውጭ ሀገር የገንዘብ ኖቶች እንዲሁም የኮንትሮባንድ እቃዎች አብረው እንደተያዙ በመግለጫው ተጠቅሷል። በተጠቀሱት ዝርዝር የሽብር እንቅስቃሴዎች ጨምሮ በተለያዩ የጥፋት ድርጊቶች ላይ ተሰማርተው የነበሩ በድምሩ 138 ተጠርጣሪዎች ከሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና ከክልል ፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በሕግ ቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉ ተመላክቷል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የሽብር እና የጥፋት ቡድኖችን ድብቅ ፍላጎት ለማክሸፍና የግንኙነት መረባቸውን ለመበጣጠስ ተጨማሪ ክትትሎችን እና ጥናቶችን እያደረገ እንደሆነ፤ በተለይም መጪው ሀገራዊ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲካሄድ አስፈላጊውን ቅድመ-ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጿል፡፡ ኅብረተሰቡም ይህን በመረዳት የተለመደውን ቀና ትብብርና ተሳትፎ በማድረግ መሰል የጥፋት ድርጊቶችን በመጠቆም ከአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ እና ከመላው የሀገራችን የፀጥታ ኃይሎች ጎን እንዲቆም ጥሪውን አቅርቧል።
ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ ይሰራል የምንለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
Apr 18, 2026 163
ወልቂጤ፤ ሚያዚያ10/2018 (ኢዜአ):-ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ ይሰራል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የጉራጌ ዞን ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ማራዘሙ ይታወቃል። ይህም በተለያየ ምክንያት የመራጭነት ካርድ ያልወሰዱ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ ዕድል ያመቻቸ ነው። የጉራጌ ዞን ነዋሪዎችም ለመራጭነት የሚያበቃቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ለሃገር ዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ ቅድሚያ ሰጥቶ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ነው የተናገሩት። በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ጋህራድ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አብዱ ሽኩር ይወክለኛል ለሃገር ሰላምና ልማት ይሰራል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ለመራጭነት እድሜው የደረሰ ዜጋ የመራጭነት ካርድ ሊያወጣ እንደሚገባ የመከሩት አርሶ አደር አብዱ፣ በድምጻቸው ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫውን እለት እየተጠባበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የወልቂጤ ከተማ ነዋሪው ወጣት አቤል ባንቀስራ በበኩሉ፣ ዴሞክራሲያዊ መብቱን በመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዱን ገልፆ፤ ሌሎችም የሱን አርአያነት በመከተል የምርጫ ካርድ እንዲወስዱ ከልምዱ መክረ ሀሳብ መስጠቱን ጠቁሟል ። በምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ልዩ ድጋፍ ለሚሹ አካል ጉዳተኞች የተሻለ ፖሊሲና አቅጣጫ ያላቸውን የፖለቲካ ፓርቲዎች እየተከታተለ መቆየቱንም አመላክቷል ። "ምርጫ የዜጎችን ተሳትፎና ፍቃድ በማግኘት በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመንግስት ስልጣን የሚያዝበት ስርዓት በመሆኑ ይበጀናል ያልነውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል" ያሉት ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ጋሻው መክብብ ናቸው ። ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ምርጫ ጠንካራና ለሁሉም የምትሆን አገር ለመገንባት መሰረት በመሆኑ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ የዜግነት ግዴታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በቀሪ ቀናትም የምርጫ ካርድ ያላወጣ ነዋሪ በምርጫ ጣቢያዎች ተመዝግቦ ካርዱን በእጁ መያዝ እንዳለበት መክረዋል። ለጠቅላላ ምርጫው እየተካሄደ ያለው የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም መራዘሙ በርካታ ዜጎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በመውሰድ የዕድሉ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 18, 2026 194
ከሚያዝያ 5 እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ በንፋስ ኃይል አማካኝነት ጨለማን ለመግፈፍ፣ ዐቅምን በለየ የቅድመ ጥናት እና ልዩ ዕቅድ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ዕውን አድርጋለች ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት 100 ሜጋ ዋት ንጹህ የኃይል አቅርቦት በመጨመር ወደ ዘርፈ-ብዙ እና ቀጣይነት ባለው የኃይል መጻዒ ዕጣ ፈንታ ለመገንባት የምናደርገውን ጉዞ ያጠናክረዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ አብነት ነው ብለዋል በወቅቱ። በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል፤ ከምንጊዜውም በላይ ታላቅ የምንሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉም አመላክተዋል። • ከኮፕ32 አስተናጋጅነት ጋር በተያያዘ ምክክር መደረጉ የኮፕ32 አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ መጀመሯን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል ሲሉ ገልጸዋል። ከግምገማ ባሻገር የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልኅቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው ብለዋል። • የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከዚያም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይትም፤ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በቅኝ ያልተገዙ፣ ለአኅጉሩ ነፃነትና አንድነት ድምፅ በመሆን ከጋራ የጽናት ታሪክ የሚመነጭ ጥልቅና ዘመናትን የተሻገረ ግንኙነት አላቸው ያሉት ጠላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም እንደ ሁሌው ኢትዮጵያ ከሰፊ ገበታዋ ያላትን ታላቅ ዐቅምና ዘላቂ ወዳጅነት አብረዋት ለሚጓዙ ሁሉ ለማካፈል ዝግጁ ናት ብለዋል። ጉብኝቱም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን የቆየ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለማስፋት ወሳኝ ምዕራፍን ከፍቷል ሲሉ ገልጸዋል። ከሁለትዮሽ ስብሰባው በመቀጠልም በሁለቱ ሀገራት በኩል ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጉዞ ያካበተችውን ልምድ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማካፈል እንዲሁም ከአጋሮቻችን የተለያዩ ዕይታዎችን በመቅሰም ለአኅጉሩ ዕድገት ዘላቂና አፍሪካዊ መፍትሔዎችን በጋራ ለማፍለቅ እንደ ወሳኝ መሠረት ያገለግላሉ ነው ያሉት። • የፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ባሳለፍነው ሳምንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ቀጣይ ትብብሮችን በምናጠናክርባቸው ቁልፍ መስኮች ላይ መክረናል ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም፤ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ፣ የተሻገረ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ በበቂ ሁኔታ ዜጎችን ሥራ ለማስያዝ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሚና አይተኬ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሥራ ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚ ያሸጋግራል፣ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሻገር እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ያገለግላል በማለት አብራርተዋል። በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነት አንዱ አንጓ ነው በማለት አስረድተዋል። የብዙ መንግሥታትና የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል። አክለውም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል። አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል። እንዲሁም የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግሥት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አብራርተዋል። ከተማ አያስፈልግኝም፤ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አመላክተዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በወሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገራችን በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ሥር እየሰደደ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሐሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል። እንዲሁም በ "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ሥራ ማስጀመራቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ማሳያ እና የወሎ የብልጽግና ተስፋ ነው ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የ"መደመር" ዕሳቤ በተግባር የታየበት፣ የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለ ሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት ነው ሲሉም ገልጸል። ያየነው ልማት የሰላም ውጤት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ በማለት፤ በአንድነት እና በትጋት ከሠራን ይህ ቀጣና የዕድገትና ብልጽግና መዳረሻ መሆኑ አይቀሬ ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንትን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት መሠረተ-ልማት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ግብዓቶችን በማመላለስ የኢኮኖሚያችን የደም ሥር፣ የብልጽግናችን መሠረት ነው ብለዋል። በዐውደ ርዕዩ የተመለከትነውም ወሳኝ የልማት ተቋሞቻችን፣ መሠረተ-ልማትን እንደ ሀገር በቅንጅትና በትብብር የመምራት አዲስ የሥራ ባህል እየገነቡ መሆናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግሥት በመንገድ፣ በኃይል፣ በመስኖ፣ በባቡርና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፍ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚሠራውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። አሁን ያለንበት ወቅት የሥራ፣ የውጤት እና የተስፋ ዘመን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ትናንት የተገነባው ለዛሬ፣ ዛሬ የምንገነባው ደግሞ ለነገው ትውልድ ኩራት እና የብልጽግና ዋስትና ነው ብለዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መሳተፍ የሚያስችለንን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል- የመዲናዋ ነዋሪዎች
Apr 18, 2026 215
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ የምርጫ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በወቅቱ በመውሰድ በምርጫው በንቃት ለመሳተፍ ዕለቱን እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ሲያካሂድ ቆይቷል። በተጨማሪም ቦርዱ የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሟል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥበት ዕለት ነው፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ድምጻቸውን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካካል አቶ ጃፋር መሐመድ እንዳሉት፤ ምርጫ ለአንድ ሀገር ዜጎች በፈቀዱትና በመረጡት መንገድ የስልጣን ሽግግር እንዲኖር በማድረግ የጋራ ዕጣ ፋንታን በጋራ የሚወስኑበት ትልቅ እድል ነው። በመሆኑን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸው፤ ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ በሽር ኢማም በበኩላቸው በሌሎች ሐሳብና ፍላጎት ስር ላለመውደቅ የምርጫ ካርድ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን ጠቅሰው፤ የመመዝገቢያው ጊዜ አልፎ ከመቆጨት ከመጸጸትን በወቅቱ መጠቀም እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። በዚህም የራስንና ቀጣይ የአገርን ሰላምና ኢኮኖሚያዊ እደገት ብሎም የዜጎችን ዘላቂ ተጠቃሚነት ማረጋጋጥ ይቻላል ብለዋል። አንድ ሀገር ልትመራ የምትችለው የራሷ መሪ ሲኖራት ነው መሪዋን ደግሞ የሚመረጠው በህዝቦቿ ነው በመሆኑም የአገሬን መሪ መምረጥ ውዴታ ብቻ ሳይሆን ግዴታዬም ጭምር ያለችን ወይንሸት ፊፋ ናት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሲያከናውን የነበረው የመራጮች ምዝገባ ማራዘሙ በተለያዩ ምክንያቶች ተመዝግበው ካርድ ለማውጣት ያልተመቻቸው ዜጎች ትልቅ እድል ነው ብላለች። ምርጫ የወደፊት ህልሜን ያሳካልኛል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ የሚረዳኝ አጋጣሚ በመሆኑ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለው ያለን ደግሞ ወጣት መሐመድ ዘይኔ ነው።
ወጣቶች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በመውሰድ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል
Apr 18, 2026 179
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በቀሪ ቀናት በመውሰድ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የክልሎች የወጣቶች ቢሮ ሀላፊዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል። ቦርዱ ለአንድ ወር የሚቆየውን የመራጮችን ምዝገባ ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አራዝሞታል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ድምጽ የሚሰጥበት ዕለት ነው፡፡ በመሆኑም መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። ከክልሎች የተወጣጡ የወጣቶች ቢሮ ሀላፊዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ምርጫ በሀገር ጉዳይ የመወሰን እድል ስለሆነ ወጣቶች ይህን ተረድተው በቀሪ ቀናት ካርድ መውሰድ ይኖርባቸዋል። ምርጫ ለሀገር እድገት እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እጅግ ወሳኝ መሆኑንም ነው የተናገሩት። ዜጎች በየጊዜው በምርጫ አማካኝነት መሪዎቻቸውን በመምረጥ፤ ይህም ይጠቅመናል ሀገርን ወደ ተሻለ ደረጃ ያደርሳል ለሚሉት እጩ የመንግስትን ስልጣን በህጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ በአደራ የሚሰጡበት ነው። በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ በሚገኘው የመራጮች ምዝገባ በመሳተፍ ካርድ ያልወሰዱ ወጣቶች ተመዝግበው ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ነው የጠየቁት። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ሱልጣን አሊ እንደገለጸው፤ በክልሉ ወጣቶች በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ በምርጫ ሂደቱ ላይ እንዲሳተፉ የማንቃት ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብሏል። ምርጫው በሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ሂደት እንዲጠናቀቅ ወጣቶች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ በንቃት በባለቤትነት ስሜት መሳተፍ አለባቸው ሲልም ገልጿል። በሲዳማ ክልል የወጣቶች ማህበር አባል በቃሉ መሰረት በበኩሉ፤ የወጣቶችን ተሳትፎ ለማጎልበት ከምርጫ ምዝገባ ጀምሮ ተሳታፊ እንዲሆኑ ከሲቪክ ማህበራትና ሌሎች አጋሮች ጋር እየተሰራ ነው። ምርጫ በሀገር ጉዳይ ላይ የመሳተፍ ብቻ ሳይሆን፤ የመወሰንም እድል በመሆኑ ወጣቶች ከምዝገባ ጀምሮ በንቃት ሊሳተፉ ነው ሲልም ተናግሯል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወጣቶች ጉዳይና በጎ ፍቃድ አገልግሎት ኮሚሽነር ወጣት ማርቆስ ማቲዎስ፤ ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመራጭነት፣ በታዛቢነት በእጩ ተወዳዳሪነት እንዲሳተፉ በተከናወኑ ስራዎች ውጤቶች መገኘታቸውን ነው የገለጸው። በክልሉ ወጣቶች ከመራጭነት ባለፈ በታዛቢነትና በእጩ ተወዳዳሪነት ተሳትፎ እያደረጉ መምጣታቸውን ተናግሯል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስከ ሚያዝያ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 46 ሚሊዮን 736 ሺህ 895 ዜጎች ለመራጭነት መመዝገባቸውን አስታውቋል።
ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጭና ፕሮግራማቸውን የሚያስተዋውቁባቸው መድረኮች መመቻቸት የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመወሰን ያስችላል
Apr 18, 2026 232
ሚዛን አማን፣ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ) -የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጭና ፕሮግራማቸውን የሚያስተዋውቁባቸው መድረኮች መመቻቸት የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመወሰን እንደሚያስችላቸው የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። አስተያየት ሰጪዎቹ በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን ተመዝግበው የምርጫ ካርድ ያልወሰዱ ዜጎች በቀሪ ጥቂት ቀናት በመመዝገብ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን መጠቀም እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ የተለያዩ የጊዜ ሰሌዳዎችን አውጥቶ ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል። ከዚህ ውስጥም ለመራጭነት የሚያበቃ የምርጫ ካርድ መውሰጃ ጊዜ ሰሌዳ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናቶች ቀርተውታል ። የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ለሀገር የሚጠቅም ፓርቲን ለይቶ ድምጻቸውን ለመስጠት ፓርቲዎች የሚያደርጓቸውን ክርክርች እና ያሏቸውን ፕሮግራሞቻቸውን በመከታተል ላይ ናቸው። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ማለቶ ታከለ እንደሚሉት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን የፐሊሲ አማራጮችን በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን በመከታተል በምርጫው ንቁ ተሳታፊ ለመሆን ዝግጅት እያደረጉ ነው ። በፌዴራል ደረጃ በቴሌቪዥን ከሚደረግ የምርጫ ማኒፌስቶ ማስተዋወቅ መርሐ ግብር ባሻገር በክልል ደረጃም መሰል ትግባራት መከናወናቸው ለመራጩ ሕዝብ በቂ ግንዛቤ እየተፈጠረለት መሆኑንም ጠቅሰዋል። ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በራስ ፍላጎት የሚያስተዳድረንን መንግስት የምንመርጥበት በመሆኑ እስካሁን የመራጭነት ካርድ ሳይወስዱ የዘገዩ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም በቀሪ ጊዜያት ካርድ ማውጣት ይገባቸዋል ሲሉም መክረዋል። ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ መምህርት አልማዝ ዓለምገና፤ በመገናኛ ብዙሃን የሚካሔዱ የፓርቲዎች ክርክሮችና የፕሮግራም ማስተዋወቂ መድረኮች በምርጫው ለሀገርና ለህዝብ ጠቃሚ ሀሳብ ያለውን የተሻለ ፓርቲን ወደ ስልጣን ለማምጣት ግንዛቤ እየፈጠሩላቸው መሆኑን ገልጸዋል ነገ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማየት አንድ ድምጽ ወሳኝ በመሆኑ በዴሞክራሲ ግንባታ፣ በልማትና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በማኅበራዊ አገልግሎቶች የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ በነጻነት ለመምረጥ ተዘጋጅቺያለሁ ሲሉ ገልጸዋል። ወቅቱ በሀገርና በፖለቲካ እሳቤዎች ላይ የሕዝብ ንቃተ ሕሊና የጨመረበት በመሆኑ ሰላማዊ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት ይኖራል ብለው እንደሚጠብቁ ነው የተናገሩት። ለአካባቢያችን ለውጥና ዕድገት ብሎም ለሀገር አንድነት መጠናከር የሚሰራ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የተናገሩት ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫው የሚሳተፉት ወጣት ታምራት አድማሱ እና አሻግሬ መቹል ናቸው። ለመምረጥ ከመዘጋጀት ባሻገር ለምርጫው ሰላማዊነትና መረጋጋት እንደ ወጣት ባለንበት አካባቢ ሚናችንን እንወጣለን ሲሉም አክለዋል።
ለሀገርና ለሕዝብ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - አርሶ አደሮች
Apr 17, 2026 1850
ደሴ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ለሀገርና ለሕዝብ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ በደቡብ ወሎ ዞን የተሁለደሬ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዘንድሮው ዓመት ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ በማውጣት የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ነው። ከዚህ ውስጥም የእጩዎች ምዝገባ የተጠናቀቀ ሲሆን የመራጭነት ምዝገባ ሂደት ደግሞ እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ/ም እንደሚካሔድም መገለጹ ይታወሳል፡፡ የወረዳው አርሶ አደሮች እንደሚሉት የምርጫ ካርድ በማውጣት በመጪው ምርጫ ላይ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት አድርገዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት ውስጥ አርሶ አደር ሰይድ ፈንታ፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ እና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። ይወክለኛል ያልኩትን ፓርቲ ወደ ስልጣን በማምጣት ሀገሪቷን እንዲመራ በካርዴ ለመወሰን እየተጠባበኩ እገኛለሁ ብለዋል። ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅም ከፀጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ነው የሚናገሩት። አርሶ አደር መሀመድ አደም በበኩላቸው፣ በምርጫው የሚጠበቀውን ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ነው የሚናገሩት። በምርጫው ቀን ይጠቅመናል፣ ይበጀናል ለምንለው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠትና የዜግነት ግዴታችንን ለመወጣት እየተጠባበቅን እንገኛለን ሲሉም ተናግረዋል። ህገ-መንግስቱ ያጎናጸፈንን መብት ከመጠቀም ባለፈ ዴሞክራሲያዊ ልምምዱ በተሻለ መንገድ እንዲከወንና ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን የድርሻችንን እንወጣለን ነው ያሉት። የመራጭነት ካርድ መውሰድ ለምንፈልገው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠት ቁልፍ ተግባር ነው ያሉት ደግሞ አርሶ አደር ሉባባ መሀመድ ሲሆኑ ካርድ ያልወሰዱ ዜጎችም በቀሪ ጊዜያት ተመዝግበው ቢዘጋጁ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። በምርጫው ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
ማህበራዊ
በአስተዳደሩ የሕጻናት መቀንጨርን ለማስቀረት የሥርዓተ ምግብ ሞዴል መንደሮችን በመመስረት እየተሰራ ነው
Apr 18, 2026 21
ሰቆጣ፤ ሚያዚያ10/2018 (ኢዜአ)፡-በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የሕጻናት መቀንጨርን ለማስቀረት የሥርዓተ ምግብ ሞዴል መንደሮች መመስረታቸውን የአስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የስርዓተ ምግብ ባለሙያ ወይዘሮ ወርቅ አያሌው ለኢዜአ እንደገለጹት በብሔረሰብ አስተዳደሩ የሚስተዋለውን የመቀንጨር ችግር ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ነው። መምሪያው ከሰቆጣ ቃል ኪዳን ስምምነት እና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የህብረተሰቡን የግብርና ምርታማነት በማሳደግ የተመጣጠነ ምግብ የመመገብ ባህሉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። እናቶች በጓሮ አትክልት፣ በዶሮና ፍየል እርባታ ሥራ ላይ ተሰማርተው ለልጆቻቸው የተመጣጠነ ምግብ እንዲመግቡ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ህጻናት ልጆቻቸውን በንጥረ ነገር የበለፀጉ አትክልት፣ ሥጋና ጥራጥሬ ምግቦችን በመመገብ ጤንነታቸው እንዲጠበቅና የተስተካከለ እድገት እንዲኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በእዚህም በአስተዳደሩ በሥርዓተ ምግብ ላይ የተሻለ እንቅስቃሴ ባሳዩ 69 ቀበሌዎች 82 ሞዴል መንደሮች መመስረቱን ባለሙያዋ ተናግረዋል። በእያንዳንዱ መንደር 60 የሚያጠቡ ነፍሰ ጡር እናቶችን በማሳተፍ ስርዓተ ምግብን በሚያሳድጉ የጓሮ አትክልትና የእንስሳት እርባታ ሥራዎች ላይ እንዲሰማሩ ተደርጓል ብለዋል። የመንደር ምስረታውን ወደ ሌሎች ቀበሌዎችና ወረዳዎች በማስፋት በሕፃናት ላይ የሚያጋጥመውን የመቀንጨር ችግር ሙሉ በሙሉ ለመፍታት በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አስታውቀዋል። በደሃና ወረዳ ዳብጦ ሞዴል መንደር ነዋሪ ወይዘሮ ገነት ደባሽ እንዳሉት በስርዓተ ምግብ ዙሪያ በተሰጣቸው ስልጠና መሰረት የጓሮ አትክልትና የዶሮ እርባታ ሥራ እያከናወኑ ነው። በእዚህም የጓሮ አትክልትና እንቁላልን ከተለያዩ ምግቦች ጋር በማሰባጠር ልጆቼን ለመመገብ ችያለሁ ብለዋል። በተደረገልን የጥቅል ጎመንና የቆስጣ ዘር ድጋፍ በጓሯችን የጓሮ አትክልት አልምተን ለመጠቀም ችለናል ያሉት ደግሞ በአበርገሌ ወረዳ የሳቃ መንደር ነዋሪ ወይዘሮ እሸሽ እሉ ናቸው። የጓሮ አትክልት ልማት ሥራቸው ልጆቻችውን የተመጣጠነ ምግም ለመመገብ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ የሕጻናት መቀንጨር ችግር ከሚስተዋልባቸው የተከዜ ተፋሰስ አካባቢዎች ውስጥ የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር አንዱ ነው። በሰቆጣ ቃል ኪዳን ስምምነት መሰረት መንግስት በሀገር በቀል መፍትሄ መሰረት ከሁለት ዓመት በታች የሆኑ ሕጻናት ላይ የሚደርሰውን የመቀንጨር ችግር በ2022 ዓ.ም ሙሉ ለሙሉ ለማጥፋት ግብ አስቀምጦ እየሰራ ነው። በዚህም በተከዜና ሌሎች አካባቢዎች ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ህጻናት፣ ነፍሰ ጡርና ወላድ ህጻናት ላይ የሥርአተ ምግብን ለማሻሻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየታየ መምጣቱን መረጃዎች ያሳያሉ። የሰቆጣ ቃል ኪዳን የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በማሻሻል የሕጻናትን ጤና፣ እድገትና ልማት ለማረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተም ይገኛል።
አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ከፍታ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋ ዲፕሎማት ነበሩ
Apr 18, 2026 25
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ከፍታ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋ ዲፕሎማት እንደነበሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለፁ። አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የአንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ በእንጦጦ ሐመረ ኖህ ኪዳነ ምህረት አንድነት ገዳም መካነ መቃብር ተፈፅሟል። በሥርዓተ ቀብሩ ላይ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ የሱፍ፣ የሀገራት አምባሳደሮችና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢዜአ እንዳሉት፤ አምባሳደር ቆንጅት በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ሀገራቸውን ያገለገሉ ብርቱ ዲፕሎማት ነበሩ። አምባሳደሯም በተለያዩ ሀገራት የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር በመሆን፣ በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ደግሞ በቋሚ መልዕክተኛነት ሀገራቸውን በታላቅ ኃላፊነት ማገልገላቸውን ገልጸዋል። አምባሳደር ቆንጂት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሥራ ዘመናቸውም ለበርካታ ዲፕሎማቶች በምሳሌነት የሚጠቀሱ ጠንካራና ታታሪ ዲፕሎማት እንደነበሩ አስታውሰዋል። በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ የከፍታ ጉዞም የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ያበረከቱ አንጋፋና የሀገር ባለውለታ ዲፕሎማት እንደነበሩ አንስተዋል። የዲፕሎማሲ ስራ በሰዓት ሳይገደብ ሙሉ ጊዜና ትኩረት በመስጠት የሚከወን እንደሆነ ያስተማሩም ጭምር መሆናቸው ጠቅሰዋል። በጡረታ ከተገለሉ በኋላም እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ከአፍሪካ ህብረት ስራዎች በዲፕሎማሲ ዘርፉ ሲያገለግሉ መቆየታቸው ተናግረዋል። አምባሳደር ቆንጂት በህይወት በነበሩበት ወቅት በርካታ ጠንካራ ዲፕሎማቶች ያፈሩ እንደነበሩ ገልፀው፤ በቀጣይም ወጣት ዲፕሎማቶች ከሳቸው ልምድና የህይወት ተሞክሮ ተምረው በመማር ሀገራቸው ለማገልገል ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥር ነው ብለዋል። አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸውተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት ማገልገላቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በ1932 ዓ.ም በሐረር ከተማ የተወለዱት አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደር በመሆን ሀገራቸውን ለረጅም ዓመታት አገልግለዋል። አምባሳደሯም በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች በባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት፤ በአፍሪካ ሕብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በቋሚ መልዕክተኛነት ሰርተዋል። ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011 ዓ.ም ደግሞ በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ልዩ አማካሪ ነበሩ።
በክልሉ ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ፈተና ውጤታማ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ ነው
Apr 18, 2026 41
ቦንጋ፤ ሚያዚያ 9/2018 (ኢዜአ)-ተማሪዎች በ12 ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤታማ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ገለጸ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ሀላፊ ደስታ ገነሜ (ዶ/ር) በክልሉ በመደበኛ፣ በማታና በርቀት 15 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች ሀገር አቀፍ ፈተና እንደሚወስዱ ገልጸዋል። ተማሪዎቹ በሃገር አቀፍ ፈተናው ውጤታማ እንዲሆኑ በፈረቃ እንዲሁም በቅዳሜና እሁድ የማጠናከሪያ ትምህርት መሰጠቱና ማታም ጥምር ቤተመጻህፍት እንዲጠቀሙ መደረጉን አንስተዋል። በትምህርታቸው የተሻሉ ወደ 2 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች በቋሚነት ትምህርት ቤት ውስጥ አድረው እንዲያጠኑ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በሚፈለገው መጠን ተማሪዎቻቸውን ወደዩኒቨርሲቲ ላላስገቡ ትምህርት ቤቶች ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት ልዩ እገዛ እየተደረገላቸው መሆኑን አብራርተዋል። ፈተናው በበይነ መረብ የሚሰጥ በመሆኑ በትምህርት ቤቶች የኢንተርኔት መሰረተ ልማት ዝርጋታና ሌሎች ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ፈተናው ውጤታማ ለመሆን ዝግጅታቸውን ማጠናከራቸውን የገለጹት ደግሞ የቦንጋ የመሀል ከተማ እና የቢሻው ወልደዮሐንስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ተማሪዎች ናቸው። በሀገር አቀፍ ፈተናው የተሻለ ውጤት ለማምጣት ዝግጅታቸውን እያጠናከሩ እንደሆነ ከገለጹ ተማሪዎች መካከል የመሀል ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተማሪ እዮብ እምሩ እና ተማሪ ፍቅራለም አቱሞ ይገኙበታል። ትምህርት ቤቱ ከመደበኛ ትምህርት ክፍለ ግዜ በተጨማሪ የሚሰጠውን የማጠናከሪያ ትምህርት በትጋት እየተከታተሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በግልና ከጓደኞቻቸውጋር በመሆን ጠንክረው እያጠኑ መሆናቸውንና የፈተና ጥያቄዎችን በመስራት ለፈተናው እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የቢሻው ወልደዮሐንስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ተግባሩ ተስፋዬ እና ተክልዬ ተሾመ እንዳሉት፣ በውጤታቸው ተመርጠው በትምህርት ቤቱ ውስጥ አድረው እንዲያጠኑ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ እድል ፈጥሯል ። በትምህርት ቤቱ የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርትና በግላቸው የሚያደርጉት ዝግጅት በሀገር አቀፍ ፈተና ጥሩ ውጤት ለማምጣት እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል። ከማጠናከሪያ ትምህርት ባለፈ ፈተናው በበይነ መረብ ለመውሰድም የቴክኖሎጂ ድጋፍና የስነ ልቦና ዝግጅት እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በትምህርት ቤቱ የባዮሎጂ ትምህርት መምህር ቆጭቶ ገብረማሪያም ተፈታኝ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በማጠናከሪያ ትምህርት ከሚደረገው ድጋፍ ባለፈ በስነልቦናም የማብቃት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የቢሻው ወልደዮሐንስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ መምህር ጌታቸው መኮንን በበኩላቸው በትምህርት ቤቱ በአዳሪና በመደበኛ 336 ተፈታኝ ተማሪዎች እንዳሉ ጠቅሰው፣ ተማሪዎቹን ለሀገር አቀፍ ፈተና ለማብቃት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ከመደበኛው ትምህርት በተጨማሪ በተቃራኒ ፈረቃና በቅዳሜና እሁድ የማጠናከሪያ ትምህርት እንደሚሰጥና በሞዴል ፈተናዎች የማለማመድ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክትል ርዕሰ መምህሩ አክለውም እንደገለጹት ተማሪዎችን በቴክኖሎጂ ብቁ ማድረግ የሚያስችል ድጋፍና በስነ ልቦናም የማዘጋጀት ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
የአምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ሥርዓተ ቀብር ተፈፀመ
Apr 18, 2026 81
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የአንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ስርዓተ ቀብር ዛሬ በእንጦጦ ሀመረ ኖህ ኪዳነ ምህረት አንድነት ገዳም መካነ መቃብር ተፈፅሟል። አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው መጋቢት 29/2018 ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸው ተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት ማገልገላቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ አመልክቷል። አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ነበሩ። አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፤ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽንም ቋሚ መልዕክተኛ በመሆን ሰርተዋል። ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011ዓ.ም ደግሞ ኢጋድ በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ላይም ልዩ አማካሪ ነበሩ።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ስኬት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉን የሚያሳልጥ ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል
Apr 18, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ስኬት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉን የሚያሳልጥ ወሳኝ ዕድል መፍጠሩን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ ገለጹ። ''ኢትዮጵያ ትገነባለች፤ ፈጠራ፣ ፍጥነትና ጥራት ለመሰረተ ልማት እመርታ'' በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሳምንት እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ሁለተኛ ቀኑን ይዞ በቀጠለው መድረክ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት ትስስርና ቀጣይ አቅጣጫ ላይ ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የኢትዮጵያን ብልፅግና የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል። እነዚህ ስኬቶችም የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ውጤታማነትን በማሻሻል አዲስ የኢኮኖሚ ዕድገት የለውጥ ምዕራፍ መክፈቱን ገልጸዋል። በቀጣይም የተቋማትን ቅንጅት በማጠናከር የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ትስስርን የሚያሳልጡ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን የኢትዮጵያ መንገዶች ግንባታ እስከ ኤክስፕረስ መንገድ ያለው ዕምቅ አቅምና ቀጣይ ተስፋ የሚል የመነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል። በጽሑፋቸውም፤ የኢትዮጵያ መንገዶች እ.አ.አ. በ1997 ከነበረበት 26 ሺህ 550 ኪሎ ሜትር በ2025 ከ180 ሺህ ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ጥራት ያለው የመንገድ መሰረተ ልማት መገንባቱን አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ የመንገድ ልማት ሽፋንም ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን በማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም የመንግስት፣ የልማት አጋሮችንና ዓለም አቀፍ ተቋማትን የበጀት ትብብር በማጠናከር እ.አ.አ በ2030 የመንገድ ሽፋንን 245 ሺህ ኪሎ ሜትር ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ህሊና በላቸው፤ የኢትዮጵያን የባቡር ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የሚዳስስ የመወያያ ጽሁፍ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የታዳሽ የኤሌክትሪክ ኃይል የባቡር መሠረተ ልማት የኢኮኖሚ ዕድትን በማፋጠን ቀጣናዊ ኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር የማይተካ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። በቀጣይም የባቡር መሰረተ ልማት ሥራዎችን የሚያፋጥን ብቁ የሰው ሃይል ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። በመድረኩ በገጠር ትስስር ዙሪያ የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት መሀመድ አሚን በበኩላቸው፤ የከተማና ገጠር ማህበራዊና ኢኮኖሚያ ትስስርን የሚያጠናክር የመንገድ መሰረተ ልማት እየተገነባ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማት ትስስር የአርሶና አርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያሳለጠ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በምስራቅ ወለጋ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 95 ሺህ ወጣቶች በተለያዩ የስራ መስኮች ተሰማርተዋል
Apr 18, 2026 67
ነቀምቴ ፤ሚያዚያ 10/2018 (ኢዜአ)፡-በምስራቅ ወለጋ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 95 ሺህ ወጣቶች ተደራጅተው በተለያዩ የስራ መስኮች መሰማራታቸውን የዞኑ የስራ እድል ፈጠራ እና ክህሎት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ባጩ ተስፋዬ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ጽሕፈት ቤቱ የሥራ አጥነትን ችግር በማቃለል የአምራች ኃይሉን የልማት ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ ይገኛል። በበጀት ዓመቱም ከ100 ሺህ የሚበልጡ ወጣቶችን በማደራጀት ወደ ሥራ ለማስገባት የታቀደ ሲሆን፣ እስካሁን ባለው ሒደት 95 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል። ወጣቶቹ ከተሰማሩባቸው መስኮች መካከል ግብርና እና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ማስገኛ ፕሮግራሞችን በአብነት ጠቅሰዋል። ወጣቶቹ በተሰማሩባቸው መስኮች ውጤታማ መሆን እንዲችሉም መንግሥት ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር እንዳመቻቸላቸው ተናግረዋል። ይህም የዞኑን ወጣቶች የሥራ ባሕል በመቀየር የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ መደላድል መፍጠሩን ገልጸዋል። በዞኑ የሲቡ ስሬ ወረዳ የንግድ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንቨስትመንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብሳ ዲለንሳ በበኩላቸው፤ ወጣቶች ከጠባቂነት ተላቀው ባላቸው ዕውቀት እና ጉልበት ሠርተው እንዲለወጡ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህ ረገድ በበጀት ዓመቱ ከ9 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለማመቻቸት ታቅዶ ሲሠራ መቆየቱን ጠቅሰዋል። ወጣቶቹን በ340 ኢንተርፕራይዞች በማደራጀት በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በእንስሳት ማደለብና እርባታ፣ እንዲሁም በሌሎች መስኮች በመሰማራት የተሻለ ውጤት በማምጣት ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል። የወረዳው አስተዳደርም ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር በማቅረብ ኢንተርፕራይዞቹ እንዲጠናከሩ ድጋፍ ማድረጉን አብራርተዋል። ከሥራ ዕድሉ ተጠቃሚዎች መካከል በብረታ ብረትና እንጨት ሥራ የተሰማራው ጪምዴሳ በዳሳ እንደሚለው፤ በዚህ ዓመት መንግሥት ባመቻቸላቸው ዕድል የ200 ሺህ ብር ብድር በመውሰድ ሥራ ጀምረዋል። በተመቻቸላቸው ዕድል ጠንክረው በመሥራትም ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻላቸውን ይናገራል። በአሁኑ ወቅትም ካፒታላቸውን ወደ 1 ሚሊዮን ብር በማሳደግ ተጠቃሚ መሆናቸውን አመልክቷል። በወረዳው የሚገኙት የጫልቱ፣ ዓለምነሽ እና ጓደኞቻቸው ማህበር አባል ወጣት ምቲኬ አበራ፤ በተያዘው ዓመት በእንጀራ ንግድ ላይ ሥራ የጀመረው ማኅበራቸው ጥሩ ገቢ ማግኘት መጀመሩን ተናግራለች።
በአምቦ ከተማ ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ሥራ ገብተዋል
Apr 18, 2026 106
አምቦ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ በአምቦ ከተማ በዘጠኝ ወራት ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ወደ ስራ መግባታቸውን የከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በአምቦ ከተማና አካባቢው በተለይም የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴውን በተመለከተ የከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጂፋራ ጫልችሳ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ከለውጡ በኋላ በዘርፉ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በርካታ ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች በመሳተፍ ለብዙ ወገኖች የስራ እድል እየፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በማኑፋክቸሪንግ፣ በአግሮ እንዱስትሪ፣ በአገልገሎት እና ሌሎችም መስኮች በብዛት እየተሳተፉ መሆኑን አንስተው፤ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራትም ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ስራ ገብተዋል ብለዋል። ከከተማዋ መዘጋጃ ቤት ጋር በመተባበር የመሰረተ ልማትና የመሬት አቅርቦት እንዲሁም ምቹ አገልግሎት እንዲኖር መሰራቱን አስታውሰው በዚህም አልሚዎች እየተበራከቱ መጥተዋል ብለዋል። በዘንድሮው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ብቻ 42 ሄክታር መሬት ለአልሚዎች መሰጠቱን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በዞኑ ሞዴል አርሶ አደሮችን ወደ ኢንቨስትመንት የማሻገር ስራ እየተሰራ ነዉ
Apr 18, 2026 106
ጅማ፤ ሚያዚያ 10/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ሞዴል አርሶ አደሮችን እና በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተዉ ስኬታማ የሆኑ ማህበራትን ወደ ኢንቨስትመንት የማሸጋገር ስራ እየተካሔደ ነዉ። በጅማ ዞን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሰፋፋ የመጣዉን የመሠረተ ልማት ግንባታ ተከትሎ በኢንቨስትመንት የሚሰማሩ ባለሀብቶች ቁጥር እየጨመረ መሆኑም ተገልጿል። በተያዘው ዓመትም 1 ሺህ 680 ፕሮጀክቶችን ወደ ስራ ማስገባቱን የዞኑ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ፅህፈት ቤት አመልክቷል። የፅህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ዘሊካ ቡላ ለኢዜአ እንደተናገሩት ፤በተያዘው ዓመት በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ 20 ማህበራት፣ 39 የህብረት ስራ ማህበራትን ጨምሮ በድምሩ 1 ሺህ 680 ፕሮጀክቶች ወደ ኢንቨስትመንት ገብተዋል። ወደ ኢንቨስትመንት ከገቡት 1 ሺህ 680 ፕሮጀክቶች ውስጥ ደግሞ 1 ሺህ 621 የሚሆኑት ሞዴል አርሶ አደሮች መሆናቸውን ነው የገለጹት፤ ወደ ኢንቨስትመንት የገቡት ባለሃብቶችም 4 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ መሆናቸዉንም ነው ያመለከቱት። ለኢንቨስትመንት ስራዉ 7 ሺህ 578 ሄክታር መሬት መሰጠቱን የገለፁት ስራ አስኪያጇ ለፕሮጀክቶቹ ተግባራዊነት ጠንካራ የሆነ ክትትልና ደጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል። በዞኑ ለኢንቨስትመንት መሬት ተረክበዉ ወደ ስራ መግባት ያልቻሉትን በመለየትም የፋይናንስ እና የሊዝ ማሽን አቅርቦት ችግር ያለባቸውን በመለየት ከባንክ ብድር የሚያገኙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየተሰራ ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም ሙያዊ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን አመልክተው አስፈላጊዉ ድጋፍ ተደርጎላቸዉ ወደ ስራ መግባት ያልቻሉ ባለሀብቶች ፍቃዳቸዉ የሚሰረዝበት አሰራር ተግባራዊ እንደሚደረግም ነው የጠቀሱት። በሌላ በኩል በተቋም ደረጃ አገልግሎት አሰጣጥን የማዘመን እና የማቀላጠፍ ስራ ትኩረት የተሰጠዉ ሲሆን ፣ ከዚህ ቀደም የነበሩ የተንዛዙ አሰራሮችን በማስቀረት የተሻለ አገልግሎት እየተሰጠ ነዉ ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቱን የዲጂታል ክህሎት አሳድጓል- የጂንካ ከተማ ሰልጣኞች
Apr 18, 2026 136
ጂንካ፤ ሚያዚያ 10/2018(ኢዜአ)፡-የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቱን የዲጂታል ክህሎት ማሳደጉን የጂንካ ከተማ ሰልጣኞች ተናገሩ። መንግስት በኢትዮጵያ የዲጂታል ክህሎት አቅምን በማሳደግ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ያለመ ስልጠና በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል እየሰጠ ይገኛል። በጂንካ ከተማ ስልጠናውን የተከታተሉ ሰልጣኞችም የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከቴክኖሎጂ ጋር በቀላሉ እንዲላመዱ እንዳገዛቸው ለኢዜአ ገልጸዋል። የከተማዋ ነዋሪ ወጣት በረከት አባይነህ በኢትዮጵያ ኮደርስ ስልጠና ከተካተቱ አራት ኮርሶች ሙሉውን በማጠናቀቅ ሰርተፊኬት መውሰዱን ገልጿል። በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ፣ በፕሮግራሚንግ እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት የስልጠና መስኮች በቂ ዕውቀት ማግኘቱን ተናግሯል። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከቴክኖሎጂ ጋር በቀላሉ እንዲላመዱ እንዳገዛቸው የገለፀችው ደግሞ ወጣት ምህረት ፍሬው ናት። ከፕሮግራሚንግ በቀር ሦስት ኮርሶችን በማጠናቀቅ ሰርተፊኬት መውሰዷን ገልፃ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቱን የዲጂታል ክህሎት በእጅጉ የሚያሳድግ ጠቃሚ ስልጠና መሆኑን ተናግራለች። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዓለም የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ከፍታ ለመረዳት ያስችላል ያለው ደግሞ ወጣት በቃሀኝ ጥላሁን ነው። በወሰዳቸው የፕሮግራሚንግ እና የዳታ አናሊስስ ስልጠናዎች ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ መጠቀም የሚያስችለውን የዲጂታል ዕውቀት ማሳደግ መቻሉን ገልጿል። መንግስት እንዲህ አይነት ጠቃሚ ስልጠናዎችን በነፃ በመስጠት ወጣቱን ብቁና ተወዳዳሪ ለማድረግ የጀመረው ጥረት ይበል የሚያሰኝ መሆኑን አንስቷል። የጂንካ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ዩኒት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ግርማ እንዳሉት በከተማ አስተዳደሩ በዘንድሮ ዓመት ከ4 ሺህ በላይ ወጣቶች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደዋል። በስልጠናው ከተሳተፉት ውስጥ 3ሺህ 26 የሚሆኑት ስልጠናቸውን ሙሉ ለሙሉ አጠናቀው ሰርተፊኬት መውሰዳቸውን ጠቁመዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሰራተኞችን የስራ ባህል አሻሽሏል
Apr 17, 2026 139
አዳማ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የሰራተኞችን የስራ ባህል ማሻሻሉን የአገልግሎቱ ስራ አስኪያጅ ገለጹ። የአዳማ ከተማ አስተዳደር የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ መኩሪያ ድንቁ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማው 138 አገልግሎቶች በመሶብ አንድ ማዕከል ውስጥ እየተሰጡ ነው። በዚህም 31 የሚሆኑ የአስተዳደሩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን በአንድ ማዕከል በማሰባሰብ የተቀናጀ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል። በማዕከሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የተቀናጀ ፈጣን አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ እየተቻለ መሆኑን ጠቁመው፤ ለተገልጋዮችም ምቹና ፅዱ በሆነ አካባቢ አገልግሎት ማግኘት ማስቻሉን ተናግረዋል። የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩ የሰራተኞችን የስራ ባህል ከመለወጡም ባለፈ የመንግስት የስራ ሰዓትን በአግባቡ የመጠቀም ዝንባሌ እየጨመረ መምጣቱንም ገልጸዋል። በማዕከሉ 18 የሚሆኑ የለሙ ቴክኖሎጂዎች በተሟላ መልኩ የኦንላይን አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የገለጹት ሃላፊው፤ የህዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሠራተኞችን አቅም በቴክኖሎጂ የማብቃት ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በከተማዋ ደረጃ ካለው ማዕከል ባለፈ በዳቤ፣ በአባ ገዳና በቦሌ ክፍለ ከተሞች የአንድ ማዕከል አገልግሎቱን ማስፋፋት ተችሏል ብለዋል። በአዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሲገለገሉ ያገኘናቸው አቶ አብረሃም ወይሴ፤ ለመሬት ጉዳይ አገልግሎት ለማግኘት ፈልገው መምጣታቸውን ገልጸዋል። የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ከመጀመሩ በፊት ችግሮች እንደነበሩ አንስተው፤ በተለይ ከአንድ መስሪያ ቤት ወደ ሌላው የሚደረገው ጉዞ እና ምልልስ ፈታኝ እንደነበር ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት ሁሉንም አገልግሎት በአንድ መስኮት እያገኘን ነው ሲሉ ገልጸዋል። ወይዘሮ አለምነሽ ሽብሩ በበኩላቸው "ከበር ጀምሮ ያለው አቀባበልና ማስተናገጃው በጣም ደስ የሚል ነው" በማለት ይገልጻሉ። በምቹ ማዕከል የተቀላጠፈ አገልግሎት በማግኘታቸው መደሰታቸውንም ተገልጋዮቹ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ያላትን ልምድ ለአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አጋራች
Apr 16, 2026 965
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ ያካበተችውን ተጨባጭ ልምድ ለአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አባላት አጋርታለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የመሩትን የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት የሚኒስትሮች ስብሰባን አስመልክቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት የሊቀ መንበርነት ሚናዋን በብቃት እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል። ዛሬ በበይነ-መረብ በተካሄደው በዚህ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ተሞክሮ ለማጋራት አመቺ ዕድል መፈጠሩን ቃል አቀባዩ አንስተዋል። ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለኢኮኖሚ፣ ለአስተዳደር እንዲሁም ለሰላምና ፀጥታ ሥራ ያለውን የጎላ ፋይዳ ለሚኒስትሮቹ አስገንዝበዋል ብለዋል። በተለይም ቴክኖሎጂው ግጭቶችን በመከላከል፣ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን በማስተላለፍ እና የሰላም ሂደቶችን በመደገፍ ረገድ ያለውን አበርክቶ አብራርተዋል። አምባሳደር ነብያት አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቅንጦት ሳይሆን ጠቃሚ የልማት መሣሪያ መሆኑን ኢትዮጵያ ተገንዝባለች ብለዋል። በዚህ ዘርፍም የተቀናጁ ተቋማትን በማቋቋም ህዝቡ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ቀልጣፋ ዲጂታል አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተሞክሮ እና በአቅም ግንባታ ረገድ እየተከናወነ ያለውን የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ በአብነት ለመድረኩ መቅረቡን ተናግረዋል። በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሻምፒዮን ሆነው መመረጣቸው፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ተሞክሮ ለሌሎች ሀገራት እንድታካፍል ትልቅ ዕድል መፍጠሩን አምባሳደሩ ገልጸዋል። አፍሪካ በቀደመው የኢንተርኔት ዘመን ዘግይታ መግባቷን ያስታወሱት ቃል አቀባዩ፤ አሁን ግን አህጉሪቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘመን ተገቢውን ቦታ በመያዝ የመሪነት ሚና እንዲኖራት ኢትዮጵያ ያላትን ጽኑ አቋም በመድረኩ ማንጸባረቋን ገልጸዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ግብ ለማሳካት የዲጂታል አስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል
Apr 16, 2026 254
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ግብ ለማሳካት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክህሎትና የዲጂታል አስተሳሰብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በለጠ እሱባለው ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ከአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ጋር በመተባበር "አመራር በሰው ሰራሽ አስተውሎት" በሚል መሪ ሃሳብ ሴሚናር አዘጋጅቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በለጠ እሱባለው በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን መገልገል ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ሆኗል፡፡ ዘመኑ የሚጠይቀውን አመራር ለመስጠት በዘርፉ ራስን ማዘጋጀት እንደሚገባ ገልጸው፤ እንደ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ያሉ ተቋማት ደግሞ ሥራቸው ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር የተያያዘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ፓርኩ በዘርፉ ልምድና አቅም ያላቸው ባለሙያዎችን በማምጣት የተቋሙን ሰራተኞችና የሥራ ሀላፊዎች ሰው ሰራሽ አስተውሎትን እንዴት መጠቀም እንዳለባቸው ግንዛቤ እንዲፈጠርላቸው እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወን የተቋሙን ግብ ለማሳካት የሰው ሰራሽ አስተውሎትን መሰረት ያደረገ ጥረት መኖሩንም ተናግረዋል፡፡ የዲጂታል ኢትዮጵያን 2030 ስትራቴጂ ግብ ለማሳካት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክህሎትና የዲጂታል አስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት ይገባል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ቦርድ ሊቀ መንበርና የአፍሪካ ቴክኖሎጂ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ባህሩ ዘይኑ፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ በመረዳት የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አቋቁማለች ብለዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ /ኤ.አይ/ ዩኒቨርሲቲ ለመክፈት በሂደት ላይ መሆኗን አስታውሰዋል፡፡ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ገዥና ተቀባይ እንደነበረች አስታውሰው፤ ፖሊሲ በማዘጋጀት የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት በመዘርጋት ቴክኖሎጂ ሰጭና ለሌሎች ሀገራት አቅራቢ ወደ መሆን ደረጃ ተሸጋግራለች ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ ተባባሪ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፕሮፌሰር ሸጋው አናጋው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በሁሉም ዘርፎች ለውጥ እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የአሰራር ለውጥ መፍጠሩን የጠቀሱት ፕሮፌሰር ሸጋው፤ የተቋማት መሪዎች በቀደመው መንገድ መምራት አይችሉም ብለዋል፡፡ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን ውጤት በሚያመጣ መንገድ ለመጠቀም የተቋማት መሪዎችን በቴክኖሎጂ ማብቃት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የዲጂታል ሽግግር ለማምጣት የአስተሳሰብና የባህል ለውጥ እንደሚያስፈልግ ገልጸው፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕውቀትና ክህሎት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል፡፡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘመን ሁኔታዎችን አስቀድሞ በመተንበይ ለውጥ በሚያመጡ ጉዳዮች ላይ አመራር ለመስጠት ክህሎት፣ ሥነ ምግባርና ሽግግር መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰላምይሁን አደፍርስ በበኩላቸው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የመሪነት ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ መንግሥት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ፖሊሲ በማውጣት ዘርፉን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በፍጥነት እያደገ ያለ ዘርፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዘርፉን እድገት የሚመጥን የመንግስት ቁርጠኝነት መኖሩን ገልጸዋል፡፡
ስፖርት
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከወራጅ ቀጠና የወጣበት ወሳኝ ድል አስመዘገበ
Apr 18, 2026 46
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ነፃነት ገብረመድህን በ38ኛው እና ፍሬው ሰለሞን በ93ኛው ደቂቃ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ32 ነጥብ ደረጃውን ከ18ኛ ወደ 14ኛ ከፍ በማድረግ ከወራጅ ቀጠና ወጥቷል። በሊጉ ሰባተኛ ድሉንም አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ34 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። ዛሬ ቀን ላይ በተካሄደ የ28ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ መቀሌ 70 እንደርታ ፋሲል ከነማን 3 ለ 0 አሸንፏል።
የዓለም አትሌቲክስ አዲስ አበባ የ2027ቱን የግራንድ ፕሪክስ ውድድር በወርቅ ደረጃ እንድታዘጋጅ ወሰነ
Apr 18, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ የ2027ቱን የዓለም አትሌቲክስ የግራንድ ፕሪክስ ውድድር በወርቅ ደረጃ እንድታዘጋጅ ተመርጣለች። የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን ውድድር የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም ዛሬ ተካሄዷል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ አጠቃላይ ዝግጅት፣ በመሰረተ ልማቱ ምቹነት፣ በውድድር ሂደቱ እና በደጋፊ የከተማችን ነዋሪ ሞራል እና ስፖርታዊ ጨዋነት በመደመም፤ አዲስ አበባ በሚቀጥለው ዓመት በፈረንጆቹ በ2027 የሚካሄደውን የግራንድ ፕሪክስ ውድድር በወርቅ ደረጃ እንድታዘጋጅ የዓለም አትሌቲክስ በዛሬው መርሐ ግብር ላይ ይፋ ማድረጉን ገልጸዋል። ከንቲባዋ ውድድሩ በወርቅ ደረጃ እንዲደረግ በመወሰኑ እንኳን ደስ አለን ብለዋል።
ሊድስ ዩናይትድ እና ቦርንማውዝ ድል ቀንቷቸዋል
Apr 18, 2026 73
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ33ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መካሄዳቸውን ቀጥለዋል። በኢላንድ ሮድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሊድስ ዩናይትድ ዎልቭስን 3 ለ 0 አሸንፏል። ኖሃ ኦካፎር እና ጀምስ ጀስቲን በጨዋታ፣ ዶምኒክ ካልቨርት-ሉዊን በፍጹም ቅጣት ምት ጎሎቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ ዘጠነኛ ድሉን ያስመዘገበው ሊድስ ዩናይትድ በ39 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ላለመውረድ በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 22ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ዎልቭስ በ17 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። ዎልቭስ በ34ኛ ሳምንት በቶተንሃም ሆትስፐርስ ከተሸነፈ ከሊጉ መወረዱ ይረጋገጣል። በሌላኛው መርሐ ግብር ቦርንማውዝ ኒውካስትል ዩናይትድን 2 ለ 1 አሸንፏል። በሴንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው ጨዋታ ማርከስ ታቫርኒየር እና አድሪያን ትሩፌርት የማሸነፊያ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሊጉ 11ኛ ድሉን ያስመዘገበው ቦርንማውዝ በ48 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት 13 የሊግ ጨዋታዎች አልተሸነፈም። በውድድር ዓመቱ 15ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኒውካስትል ዩናይትድ በ42 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከብራይተን፣ ቼልሲ ከማንችስተር ዩናይትድ ምሽት አራት ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
ዛሬ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድርን በአዲስ አበባ በድምቀት አስተናግዳለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Apr 18, 2026 131
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ ዛሬ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድርን በአዲስ አበባ በድምቀት ማስተናገዷን ከንቲባ አዳነች አበቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ይህ ስኬት በከተማችን የገነባናቸው ዘመናዊ የስፖርት መሠረተ ልማቶች ውጤት ከመሆኑም ባለፈ፣ አገራችን በአትሌቲክስ ዘርፍ ያላትን ታላቅ ዝና ዳግም ያረጋገጠ ነው ብለዋል። በሚያዝያ ወር ብቻ የምናስተናግዳቸው ሦስት ታላላቅ ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ኩነቶች፣ ከተማችን ማንኛውንም ዓይነት ዓለም አቀፍ ውድድር የማስተናገድ ብቃትና ደረጃ ላይ መድረሷን የሚያሳዩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል። እነዚህ ውድድሮች ተተኪ አትሌቶችን ከማነቃቃታቸውም በላይ ለስፖርታዊ ቱሪዝም ዕድገት የጎላ ፋይዳ አላቸው። ይህ ታሪካዊ ውድድር በአዲስ አበባ መካሄዱ ከተማችንን ለነዋሪዎቿ ምቹና ሳቢ ከማድረግ ባለፈ፣ ለዓለም አቀፍ ኩነቶች ማራኪ የስበት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን በተግባር ያሳየ እውነት ነው ሲሉም ገልጸዋል። ውድድሩ በስኬት እንዲጠናቀቅ የተለመደውን ኢትዮጵያዊ ጨዋነትና እንግዳ ተቀባይነት ላሳዩት ስፖርት ወዳድ ነዋሪዎችም በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል። ለእንግዶቻችን በቆንጆዋ አዲስ አበባ የማይረሳና ያማረ ቆይታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ብለዋል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባስተላለፉት መልዕክት።
አካባቢ ጥበቃ
ኮፕ 32 ዘላቂ ትሩፋት ያለው ሆኖ እንዲያልፍ ለማድረግ ይሰራል - ዓለምጸሐይ ጳውሎስ
Apr 18, 2026 150
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2018 (ኢዜአ)፦ 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ32) ሂደት ዘላቂ የሆነ ትሩፋት ያለው ሆኖ እንዲያልፍ ለማድረግ እንደሚሰራ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሐይ ጳውሎስ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ32ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ32) ብሔራዊ ኮሚቴ የተከናወኑ ሥራዎችን ገምግመዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምጸሐይ ጳውሎስ በዚሁ ወቅት የኮፕ32 መሠረተ ልማት፣ ሎጂስቲክስ እና ኦፕሬሽን ግብረ ኃይል የተከናወኑ ተግባራትን እና ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮችን በሚመለከት ለኮፕ32 ብሔራዊ ኮሚቴ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም የግብረ ኃይሉ ዓላማ ጉባዔው ከመካሄዱ በፊት አስፈላጊ የሆኑ ጉዳዮችን በማሟላት፤ ጉባዔው በሚካሄድበት ወቅት የተሳለጠ እንዲሆን እንዲሁም ከተጠናቀቀ በኋላ ትውልድ ተሻጋሪ የሆነ ዕሴት አሳርፎ ማለፍ እንዲችል ማድረግ ነው ብለዋል። በዚህም ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እና መስፈርቶችን የሚያሟሉ መሠረተ ልማቶች የሚገነቡ እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚሰባሰቡ አስፈላጊ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቁመዋል። ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ የተሳለጠ እና ስኬታማ ጉባዔ ከማካሄድ በተጨማሪ ወደ ትውልድ መሻገር የሚችሉ፣ ዘላቂ እና ለቀጣይ ስራዎች አጋዥ የሚሆኑ መሠረተ ልማቶች መገንባትን ታሳቢ ያደረገ ዓላማን በመያዝ እየተሰራ ነው ብለዋል። ግብረ ኃይሉ መሠረታዊ የሚባሉ ግቦችን በመለየት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸው፤ የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን የሚያሟሉ እና ጉባዔውን የሚያሳልጡ መሆናቸውን ማረጋገጥ የመጀመሪያው ግብ መሆኑን አመላክተዋል። የተገነቡ መሠረተ ልማቶች እንግዶች በጉባዔው ለመሳተፍ ሲመጡ ከአቀባበል ጀምሮ እስከሚሸኙበት ጊዜ ድረስ ደረጃውን የሚመጥን እንቅስቃሴዎች እንዲኖሩ በማድረግ ስኬታማ ጉባዔ እንዲካሄድ መሠረታዊ ጉዳዮችን የያዘ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ሂደት ነባሩ የከተማ እንቅስቃሴ እና የሕብረተሰብ አገልግሎት እንደተጠበቀ ሆኖ ነባሩን ሳይረብሽ አዲስ የሚመጣውን መቋቋም የሚችል የማይበገሩ መሠረተ ልማቶች መኖራቸውን የማረጋገጥ ግብ ሌላኛው ትኩረት የተደረገበት እንደሆነ መግለጻቸውን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል። በሂደቱ የሚፈጠሩ አቅሞች በተለይም ወጣቶች በሂደት ውስጥ እንዲያልፉ በማድረግ የሀገር ውስጥ አቅምን መገንባት የሚያስችል ስራ እንደሚሰራም አብራርተዋል። በተጨማሪም ሙሉ ሂደቱ ዘላቂ የሆነ ትሩፋት ያለው ሆኖ እንዲያልፍ ማድረግን ታሳቢ በማድረግ እንደሚሰራ ገልጸው፤ ጉባዔው ከተለያዩ ጉዳዮች አኳያ ደኅንነቱ የተጠበቀ ሆኖ እንዲካሄድ የሚያስችል ግቦችን በመያዝ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዞኑ የበጋ ወራት የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራዎች ምርታማነት እንዲጨምር አድርገዋል
Apr 18, 2026 89
አዳማ፤ ሚያዚያ 10/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የበጋ ወራት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ምርታማነት እንዲጨምር ማድረጋቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የጽህፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንዳስታወቁት በዞኑ በየዓመቱ የተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች የአካባቢ መራቆትን ከማሻሻል ባለፈ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎቹ የውሃ ምንጮች እንዲጎለብቱ በማድረግ ለመስኖ ልማት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አስረድተዋል። የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራው የአፈር ለምነት እንዲጨምር እና በጎርፍ ይጠረግ የነበረን ለም አፈር በማስቀረት የግብርና ምርታማነት እንዲጨምር ማድረጉን አስረድተዋል። የአፈርና ውሃ እቀባ ሥራዎች በተከናወነባቸው ተፋሰሶች ላይ በክረምቱ ወራት ችግኞችን በመትከልና በመንከባበከብ ህብረተሰቡ በእንስሳት ማድለብ፣ በንብ ማነብ፣ በፍራፍሬ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆን በቅንጅት መሰራቱንም አውስተዋል። በስራውም አርሶ አደሮች፣ ወጣቶችንና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን ጠቅሰዋል። የልማቱን ውጤታማነት ለማስቀጠልም በዘንድሮው የበጋ ወራት በ270 ተፋሰሶች ላይ የተለያዩ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች በጠንካራ የህዝብ ተሳትፎ ማከናወን ተችሏል ብለዋል ከተከናወኑ ተግባራት በዋናነት 54 ሺህ 693 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የተለያዩ የእርከን ሥራዎች መሰራታቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። ከዚህም በተጨማሪ ሰፋፊ የእርጥበት ማቆያ መዋቅሮችን ጨምሮ የተለያዩ ስነ-አካላዊ እና ስነ-ሕይወታዊ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችን በስፋት መከናወናቸውን አቶ አብነት ጠቅሰዋል። የዞኑ አርሶ አደሮች የተፋሰስ ልማት ስራ ጠቀሜታውን በመረዳታችን በየዓመቱ ለአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራው ልዩ ትኩረት ሰጥተው መሳተፋቸውንም አንስተዋል። በአካባቢያቸው በተሠራው የተፈጥሮ ሀብት ሥራ ጎርፍን በመከላከልና የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ለሰብል ምርታማነት ጉልህ አስተዋጾ እያደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።
በግብርናው ዘርፍ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል
Apr 17, 2026 86
ደዋጨፋ፤ሚያዚያ 9/2018(ኢዜአ)፡-የክልሉን ሰላም በማጽናት በግብርናው ዘርፍ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለፁ። የፌዴራል፣ የአማራና የአፋር ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ዳዋጨፋ ወረዳ በኩታ ገጠም የለማ የፍራፍሬ ችግኝ ተከላን ዛሬ አስጀምረዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ የክልሉን ሰላም በማጽናት የህብረተሰቡን ሁለተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ ነው። በተለይም በግብርውና ዘርፍ ዘመናዊ ቴክኖሎጂንና የተሻሻለ አሰራርን በመተግበር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት ሁሉን አቀፍ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በክልሉ አካበቢን መሰረት ያደረገ የልማት አቅጣጫ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመው ዛሬ የተጀመረው ኩታገጠም የፍራፍሬ ልማትም ይህንኑ ከግምት ያስገባ ነው ብለዋል። የተጀመረውን የፍራፍሬ ልማት ወደ አፋር ክልል አጎራባች ወረዳዎች በማስፋት ጥራት ያለው የፍራፍሬ ምርትን ከአገር ውስጥ አልፎ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሀጅ አወል አርባ በበኩላቸው የሁለቱን ክልል የህዝብ ለህዝብ ትስስር በልማትም አጠናክሮ ለማስቀጠል ቁርጠኛ አቋም ተወስዷል ብለዋል። በዚህም ዛሬ የተጀመረው የፍራፍሬ ልማት የሁለቱን ክልሎች አዋሳኝ ወረዳዎችን አካቶ በመተግበር የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነም ገልፀዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር)፣ በሀገሪቱ ሁሉም ክልሎች ያለውን ፀጋና ሀብት በጥናት ለይቶ በማልማት ለሀገር ብልፅግና ለማዋል ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። በግብርናው ዘርፍ በጥራት፣ በአይነትና በብዛት በማምረት ከፍጆታ አልፎ ለወጭ ንግድ የሚተርፍ አመራረት ላይ በማተኮር ውጤት እየተገኘ መሆኑንም ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየታየ ያለው ኩታ ገጠም የፍራፍሬ ልማት ለአገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት ድርሻው የጎላ እየሆነ መምጣቱን አስረድተዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን የበልግ ወቅት የችግኝ ተከላ ሥራ ተጀመረ
Apr 17, 2026 95
ዲመካ፣ ሚያዚያ 9/2018 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ኦሞ ዞን በተያዘው የበልግ ወቅት ከ4 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ሀገር በቀል ችግኞች ተከላ ሥራ መጀመሩን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በዞኑ የ2018 ዓ.ም የበልግ ወቅት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ተከላ ዛሬ በዲመካ ከተማ ተጀምሯል። የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ምንላርገው አዲሱ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በዞኑ በዘንድሮ የበልግ ወቅት ከ4 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ሀገር በቀል ችግኞች ይተከላሉ። ህዝቡን በማሳተፍ ለሚከናወነው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ከ2 ሚሊዮን በላይ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ተዘጋጅተው ዛሬ የመትከል ሥራው በይፋ መጀመሩን ተናግረዋል። የችግኝ ተከላ ሥራው ከአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ጎን ለጎን እንደሚካሄድ ገልጸው፣ ለግጦሽ ሣር የሚሆን ሥፍራን የመከለል ሥራም አብሮ ይከናወናል ብለዋል። እንደኃላፊው ገለጻ ዘንድሮ የሚተከሉት ችግኞች የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የሚያግዙ፣ ለምግብነት እና ለገቢ ምንጭነት የሚውሉ ፍራፍሬዎች እንዲሁም ለጥላነት የሚያገለግሉ ናቸው። በደቡብ ኦሞ ዞን ዲመካ ከተማ ዛሬ በተጀመረው የበልግ ወቅት የአረንጓዴ አሻራ መርሀሃ ግብር ችግኝ ተከላ ላይ የተሳተፉት አቶ ናደው ኤካደ በበኩላቸው በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ቀደም ሲል የተተከሉ ችግኞች ለተፈጥሮ አደጋ የነበራቸውን ተጋላጭነት እንደቀነሱላቸው ተናግረዋል። ልማቱ ያለውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም በአግባቡ በመረዳታቸው በተያዘው የበልግ ወቅትም ሆነ በመጪው የክረምት ወቅት በሚካሄድ የተከላ መርሀግብር የሚያደርጉትን ተሳትፎ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎች እና የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄዎች ተጨባጭ ውጤት እንዳመጡ የጠቀሱት ደግሞ አቶ ስጦታው አመዴ ናቸው። የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎች በተሰሩባቸው አካባቢዎች ተጨባጭ ለውጦች እንደመጡ ገልጸው፣ በተለይ ተራቁተው በነበሩ አካባቢዎች ችግኝ በመተከሉ እያገገሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 446
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 360
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 650
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት። ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው
Mar 22, 2026 343
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሐተታዎች
የጤና ነገር …
Apr 17, 2026 219
በዮሐንስ ደርበው ማዲያት ታክሞ ይድናል? እነማንንስ ያጠቃል? የሥነ-ውበት ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ሱመያ ኑርሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለማዲያት መንስዔ፣ ምልክቶች እና ሕክምና ሙያዊ ሐሳባቸውን አጋርተዋል። እንደ ባለሙያ ቢደረግ ያሉትንም መክረዋል። • ማዲያት እነማንን ያጠቃል? ማዲያት ማንኛውንም ሰው እንደሚያጠቃ ያነሱት ዶ/ር ሱመያ፤ በብዛት ግን በሴቶች ላይ እንደሚከሰት ያስረዳሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ እርግዝና ላይ ያሉ እንዲሁም የወሊድ መከላከያ የሚወስዱ ሴቶች እና ሆርሞናል ቴራፒ ላይ ያሉ ሰዎች በስፋት ለማዲያት ተጋላጭ ናቸው። በተጨማሪም በብዛት ምግብ ማብሰል (ኪችን) ላይ የሚሠሩ ሰዎች ለማዲያት እንደሚጋለጡ ጠቁመዋል። ባብዛኛው ማዲያት የሚያጠቃው በዕድሜ ከ25 ወይም ከ30ዎቹ በላይ የሆኑትን መሆኑንም አንስተዋል። • መንስዔ እንደ ዶክተር ሱመያ ገለጻ፤ ለማዲያት ከሚያጋልጡ መንስዔዎች መካከል ዋነኛው የፀሐይ ጨረር ነው። በተጨማሪም ሆርሞናል ፋክተር (የወሊድ መከላከያ መጠቀም፣ እርግዝና ላይ መሆን፣ ሆርሞናል ቴራፒ መውሰድ) ለማዲያት አጋላጭ መንስዔ ሆነው ይጠቀሳሉ ይላሉ። ጭንቀት እንዲሁም ቆዳን የሚያስቆጡ ነገሮች ለማዲያት አጋላጭ መሆናቸውንም ነው ያብራሩት። • ምልክቶች ማዲያት ቀላ፣ ጠቆር ወይም ደብዘዝ ያለ ቀለም (መልክ) ይዞ ከትንሽ ጀምሮ የሚሰፋ መሆኑን ዶክተር ሱመያ አስገንዝበዋል። ለምሳሌ ይላሉ፤ ጉንጭ ላይ መውጣት ቢጀምር ወደ ሁለቱም ጉንጮች ከዚያም ወደ ግንባር እንዲሁም አገጭ እና አፍንጫ ሊደርስ እንደሚችል ገልጸዋል። በሂደትም የማቃጠል፣ የመቆጥቆጥ እና ማሳከክ ሁኔታ ሊኖረው እንደሚችል ነው ያነሱት። • ሕክምና መንስዔዎቹን ዐውቆ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ያስገነዘቡት ዶክተር ሱመያ፤ የፀሐይ ጨረር መከላከያዎችን መጠቀም፣ በሕክምና የሚሰጡ መድኃኒቶችን ሳያቋርጡ በትዕግስት መጨረስ (ቶሎ ለውጥ አላየሁበትም ብሎ አለማቋረጥ) እንደሚገባም መክረዋል። የማዲያት ሕክምና ስኬታማነቱ ለሁሉም ሰው በዕኩል ጊዜ እንደማይታይ በመግለጽ፤ እንደተከሰተበት ጊዜ ከሰው ሰው እንደሚለያይ በአጽኦት ተናግረዋል። ለምሳሌ አሉ፤ ዓመታት ያለፉት ማዲያት እና 2 ወራት የሆኑት ሕክምና እኩል ቢጀመርም በተመሳሳይ ጊዜ ላይድኑ እንደሚችሉ አመላክተዋል። ስለዚህ የሌላኛው ድኖ የኔ አልዳነም በሚል ሕክምናን ማቋረጥ ስህተት መሆኑንም ነው ያስረዱት። በሌላ በኩል ማዲያትን አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አረጋግጠው፤ ይህም የሚሆነው መንስዔዎቹን በማወቅ የማዲያት ተጋላጭ ባለመሆን ነው ብለዋል። ከተቻለ በየሥድስት ወሩ ወይም በየዓመቱ የቆዳ ጤና ምርመራ ማድረግ እና ያለበትን ደረጃ ማወቅም የሚከሰት ችግር ቢኖር እንኳ ሥር ሳይሰድድ በማከም ቶሎ እንዲድን ማድረግ ይቻላል ነው ያሉት።
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 13, 2026 207
በምግብ ራስን የመቻል ጉዞ አንዱ ምሰሶ - የስንዴ ልማት በሙሴ መለሰ ስንዴ በኢትዮጵያ በከፍትኛ ደረጀ ከሚመረቱና ለግብይት ከሚውሉ የሰብል ምርቶች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የስንዴ አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል በግንባር ቀደምነት ትጠቀሳለች። ከ2011/2012 የምርት ዘመን በፊት ኢትዮጵያ በመኸር የምታለማው ስንዴ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊየን ሔክታር ያልበለጠ ነበር። የበጋ መስኖ ስንዴ ሲጀመርም 3 ሺህ ሔክታር ብቻ እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በመኸር፣ በበጋ መስኖ እና በበልግ ወቅት 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ እያለማች እንደምትገኝ የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያስረዳል። ሚኒስቴሩ የ2018 ዓ.ም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፤ 4 ነጥብ 29 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ በማልማት ከበጋ መስኖ ስንዴ 175 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን መግለጹ ይታወሳል። በኢትዮጵያ በአብዛኛው የስንዴ ምርት የሚመረተው በአነስተኛ አርሶ አደሮች ነው። ባለፉት ዓመታት ግን የሜካናይዝድ እርሻ የስንዴ ምርቱን በእጥፍ እንደጨመረው ይገለጻል። መንግሥት መስኖን በመጠቀም ስንዴን በዓመት አንድ ጊዜ ከማምረት ወደ ሦስት ጊዜ ማምረት የሚቻልበትን አሰራር በመፍጠር የሀገሪቱን ምርታማነት ለማሳደግ እየሠራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ107 ሚሊየን ኩንታል በላይ ነው። ይህንን ፍላጎቷን ለመሙላት ለዓመታት ከ700 ሚሊየን ዶላር እስከ 1 ቢሊየን ዶላር ለስንዴ ግዥ ወጪ ታደርግ ነበር። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ትሸፍን የነበረውም ከውጭ በምትገዛው ስንዴ ነበር። መንግሥት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በማስፋፋትና በየዓመቱ የሚመረትበትን ዙር በመጨመር ኢትዮጵያ የስንዴ ፍጆታዋን ሙሉ በሙሉ እንድትሸፍን በትኩረት ሲሠራ ቆይቷል። በዚሁ በ2014 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገር ስንዴ ማስገባት አቆመች። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያገኘችው ውጤት ከውጭ ማስገባትን ማስቆም ብቻ አልነበረም። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ራስን ብቻ ሳይሆን ኤክስፖርት የማድረግ ዐቅም እንዳላት በመግለጽ፤ ስንዴ ወደ ውጪ መላክ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስቀመጡት ሀገራዊ ግብ መሰረት ኢትዮጵያ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ውጭ የመላክ ተግባርን በይፋ አስጀምራለች። የስንዴ ኤክስፖርቱ ኢትዮጵያ ገጽታዋን የሚለውጥ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ መግባቷን የሚያመላክት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ገልጸው ነበር። ኢትዮጵያ በ2015 ዓ.ም የሀገር ውስጥ ፍጆታዋን ሸፍና 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ለውጭ ገበያ የማቅረብ ዐቅም እንዳላት ብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚና የኤክስፖርት ኮሚቴ አረጋግጧል። ኮሚቴው የሀገራዊ የነፍስ ወከፍ ፍጆታና የሀገሪቱን አጠቃላይ የምርት ሚዛን በማጥናት ከፍጆታ የሚተርፍ 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ወደ ውጭ መላክ እንደሚቻልም ተገልጿል። 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ባሳለፍነው የካቲት ወር በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄዱ የሚታወስ ነው። በወቅቱም የአፍሪካ ሕብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ከጉባዔው ጎን ለጎን በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ ተምሳሌታዊ የሆነ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ የስንዴ ምርታማነቷን በማሳደግ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈን ባለፈ ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሏን ሕብረቱ መመልከት መቻሉንም ተናግረዋል። የአፍሪካ ሀገራት በዓመት ውስጥ ለምግብ ምርቶች ከሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ ስንዴ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዝም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከውጭ የሚገባውን ምርት በሀገር ውስጥ ስንዴ መተካት እንደሚቻል በተግባር ያሳየችበት መንገድ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የኢትዮጵያን ተሞክሮ ወስደው ወደ ተግባር እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ሥራ ላይ እያሳየች ያለውን ሥራ አስፍታ ከቀጠለች በምግብ ራሷን የመቻል ሕልሟን የማሳካት እድሏ ሰፊ መሆኑንም ማመላከታቸው ይታወሳል።
የጤና ነገር ...
Apr 3, 2026 2160
በዮሐንስ ደርበው የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። የኒውትሬሽን ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ የሰው ልጅ የሰውነት ክፍል 60 በመቶው ውኃ እንደመሆኑ ለተስተካከለ ጤና ሚዛን መጠበቅ በቂ ውኃ መጠጣት ይገባል። ውኃን በትክክለኛው መጠንና ጊዜ መውሰድ ከተቻለ የኩላሊት ህመም ተጋላጭነትን 50 በመቶ መቀነስ እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ነገር ግን ሰውነት የሚፈልገውን የውኃ መጠን በአግባቡ ካላገኘ ለዕለታዊ እና በጊዜ ሂደት ሥር ለሚሰድዱ ህመሞች የመጋለጥ ዕድል እንደሚጨምርም ያነሳሉ። ለመሆኑ ሰውነት የሚፈልገውና በቂ የውኃ መጠን የሚባለው መጠኑ ስንት ነው? በቂ ውኃ አለመጠጣትስ የሚያስከትለው ችግር ምንድን ነው? በሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎች ላይ የኒውትሬሽን መምህር፣ ተመራማሪ እና ደራሲ ይሁኔ አየለ ምላሽ አላቸው። አንድ ሰው የሚያስፈልገው የውኃ መጠን በዕድሜ፣ ጾታ፣ በሥራ ባሕርይ፣ በመኖርያ አካባቢ፣ እንደ ጤና ሁኔታው እና እንደ ሰውነት ክብደቱ እንደሚወሰንም በምላሻቸው አስገንዝበዋል። ለምሳሌ የስኳር ታማሚዎች፣ የምታጠባ እናት፣ በዕድሜ የገፉ ሰዎች፣ ብዙ አድካሚና ላብ የሚያወጡ፣ በሞቃታማ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች በቀን 3 ሊትር ውኃ መጠጣት አለባቸው ይላሉ። በአማካይ ግን በቀን አንድ ሰው ከ2 እስከ 3 ሊትር ውኃ መጠጣት እንደሚጠበቅበት ይገልጻሉ። ጤናማ ሕይወት የሚመሠረተው ከውኃ ነው፤ ለምሳሌ ውኃማውን 60 በመቶ የሰውነት ክፍል ሚዛን ለማስጠበቅ የግድ አስፈላጊውን መጠን ውኃ መጠጣት እንደሚገባ ይመክራሉ። በሰውነት ውስጥ የሚካሄደው ሕይወታዊ ሂደት (ባዮሎጂካል ፕሮሰስ) ውኃን መሠረት ያደረገ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለምሳሌ ለተስተካከለ የሥርዓተ-ምግብ ሂደት፣ ቆሻሻን ከሰውነት አጣርቶ ለማስወጣት፣ የአጥንት መገጣጠሚያ ሥራን ለማስተካከል እና ለሌሎችም በርካታ የሰውነት ክፍሎች የተሳለጠ ተግባር ውኃ ቁልፍ መሆኑን አንስተዋል። ይህን ተከትሎም ውኃ ካሎሪ አልባው መድኃኒት (ተፈጥሯዊው መድኃኒት) እስከመባል መድረሱን ነው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ያስረዱት። ሰውነት የሚያስፈልገውን ያህል ውኃ አለመጠጣት ግን ድካም ያስከትላል፤ ለማየት፣ ለመንቀሳቀስ፣ ለመሥራት፣ ለማሰብ፣ ለመረጋጋት . . . አያስችልምና ሲሉ ያብራራሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንድ ሰው ውኃ የመጠማት መጠኑ ከአራት በመቶ በላይ ከሆነ ለሞት ሊጋለጥ እንደሚችልም ጠቅሰዋል። ውኃ አለመጠጣት፤ የጨጓራ ህመምን በማባባስ ማስገሳት፣ የቆዳ ድርቀትና ግርጣት፣ የኩላሊት ህመም ሌሎች የሰውነት ክፍሎችም ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሠሩ ያደርጋል ነው ያሉት። ከምግብ በፊት 30 ደቂቃ ቀድሞ ውኃ መጠጣት ውፍረትን ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በቂ ውኃ ከመጠጣት በተጨማሪ ፍራፍሬዎችንና አትክልቶችን ማዘውተር እንደሚመከርም ገልጸዋል። የፈላ ውኃ እና የዝናብ ውኃን በብዛት መጠጣት በሰውነት ውስጥ ያሉ ንጥረ ነገሮችን በማስወገድና በኩላሊት ላይም ጫና እንደሚፈጥር አመላክተዋል። ለተስተካከለ ጤናማ ሕይወት የግድ ውኃ መጠጣትን ልማድ ማድረግ እንደሚገባም ይመክራሉ። #ውኃ_መጠጣት #ጤና #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency
ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች
Apr 3, 2026 2275
በዮሐንስ ደርበው የለውጡ መንግሥት ኢትዮጵያን ማሥተዳደር ከጀመረ እነሆ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ላይ 8 ዓመት ሞላው። በእነዚህ ዓመታት በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚው፣ በማኅበራዊ ዘርፉ በዲፕሎማሲውና በሌሎችም መስኮች የተለያዩ ስኬቶች ተከናውነዋል። በእነዚህ ጥቂት ዓመታትም ለማሳካት ቀርቶ ለማሳብ የማይደፈሩ ብዙ ውጤቶችም ተመዝግበዋል። የተገኙት ስኬቶች ከጊዜያቸው የፈጠኑ ናቸው። ለዚህም ሕዝቡ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በነቂስ እየወጣ አድናቆቱን ገልጿል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሰጡት የሰላ አመራርነትና ቁርጠኝነትም አክብሮቱንና ምሥጋናውን ገልጿል። የለውጡ መንግሥት አካሄድ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የልማት ፕሮጀክቶችም በይበልጥ ተስፋፍተውና ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መንግሥት ለሚያደርገው ጥረት ከጎኑ እንደሚቆሙም በድጋፍ ሰልፍ ላይ ባስተጋቧቸው መልዕክቶቻቸው አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ በለውጡ መንግሥት ለማሳካት ቀርቶ ለማሰብ የማይደፈሩ ተግባራት ተከናውነዋል። ከእነዚህ ከፍተኛ ጥቅም ከተገኘባቸው የታሪክ እጥፋትን ካሠረጹ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል ጥቂቶቹን ቀጥለን በወፍ በረር እንዳሥሣለን። ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ሥልጣኔ - በምርጫ ካርድ መምረጥ የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። • የኮሪደር ልማት እንደምናውቀው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነትና ልዩ ትኩረት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከሁሉም አስቀድሞ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ ነው። አሁን ላይ ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የበርካታ ከተሞችን ገጽታ የቀየሩ አስደማሚ ሥራዎች ተከናውነውበታል። ይህም በገጠር ጭምር ተጠናክሮ የቀጠለ ጉዳይ ነው። ለዘመናት አሮጌ ገጽታዋን ይዛ ያሸለበችውን አዲስ አበባ እንደ አዲስ የፈጠራትም ይኸው ፕሮጀክት ነው። አሁን ላይ መዲናይቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን ለውጥ ዐይተው ዝም ማለት አልቻሉም። ከመደመማቸው አንጻር የዘወትር አጀንዳቸውም እያደረጓት ይገኛሉ። ይህንን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት፤ ኮሪደር ልማት ማለት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት ነው ማለታቸው ይታወሳል። ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑንንም አስረድተዋል። ከለውጡ መንግሥት ዐበይት የትኩረት መስኮች አንዱ የሆነውን የቱሪዝም ዘርፉን እንቅስቃሴ ለማሳደግም ቁልፍ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ ድርብርብ ፕሮጀክት ነው የኮሪደር ልማት። • የበጋ መስኖ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የለውጡ መንግሥት ዋነኛ ትኩረቱ ነው። ለዚህም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አንዱ ማሳኪያ ሥልት አድርጎ እየተጋ ይገኛል። የበጋ መስኖ ስንዴ ኢትዮጵያ ስንዴን ከውጭ ማስገባት አቁማ መላክ እንድትጀምር ያስቻለ ኢኒሼቲቭ ነው። በዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችና በሜካናይዜሽን ታግዞ በስፋት እየተሠራበትም ይገኛል። ከለውጡ መንግሥት ወዲህ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ምክንያት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በምርታማነት ማደግና የሥራ ዕድል በመፍጠር አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብም ከፍተኛ ውጤት ተገኝቶበታል። ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ ስንዴ ላይ ባሳየችው ትጋት፤ ፍጆታዋን በራሷ ዐቅም የሸፈነችው፣ ስንዴን ከውጭ ማስገባትን ያቆመችው፤ ስንዴን ወደ ውጭ መላክ የጀመረችው በለውጡ መንግሥት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ በመሸለም ለጥረታቸው ዕውቅና መስጠቱም ይታወሳል። • መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀደም ሲል አንድ ጉዳይን ለማስፈጸም እዚያም እዚህም መንከራተት የግድ ነበር። በዚህ አያበቃምና ወረፋውም ሌላ ችግር ነው። መንግሥት በተለያዩ መድረኮች ባካሄዳቸው ሕዝባዊ ውይይቶች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉልን የሚሉ እሮሮዎች በረከቱ። መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል ሥራ ወደ ተግባር አሥገባ። በዚህም መሠረት ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ ጀመረ። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነውም አሉ። ለዚህ ቁርጠኝነታችን አንዱ ማሳያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመራቸውንም ገለጹ። እንግዲህ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ አንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ ታግዘው በተሳለጠ ሂደት እንዲሰጡ በማድረግ የተገልጋይን እንግልት፣ ገንዘብ እና ጊዜ መቀነስ ያስቻለ አሠራር ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት ተደርጎም ይወሰዳል። በየከተሞቹም እየተስፋፋ ነው። • አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ አይ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ተጠቃሚ እንድትሆን ከፍተኛ ጉጉት እንዳላቸው በቁጭት በተለያዩ መድረኮች ያነሳሉ። ለዚህም መፍትሔ ዘይደው ተቋማትን ከማቋቋም ጀምሮ ለዘርፉ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ ተግተዋል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂው ጋር አብሮ ለመጓዝ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን አቋቋመች። የኤ አይ ዩኒቨርሲቲ በመክፈት በግብርናው፣ በጤናው እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠርም በሂደት ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት ቀይሮ ወደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ሕንፃ በተዛወረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአምስት ዓመት ውስጥ አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ መድረሱ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ የሮቦቶችን ሶፍትዌር ብቻ ሳይሆን ውጫዊ የአካል ክፍልን (ሃርድዌር) መሥራት ጀምሯል ብለዋል። ድሮን ማምረት ብቻ ሳይሆን የማነጋገር ዐቅም እየፈጠረ ያለ ተቋም መሆኑንም አንስተዋል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ደረጃ የሚወዳደር አሠራርን የሚከተል መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ምርቶችን አውጥቷል ማለታቸው ይታወቃል። ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮሉሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን ሲሉ ማስገንዘባቸውም ይታወሳል። • የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው። በዚህ ሂደት ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊታአውራሪነት ይጠቀሳል። በተደራጀና ተቋማዊ ሆኖ ባልተቆራረጠ አካሄድ እየተከናወነ ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተተከሉ ችግኞችም በየዘርፉ ተጠቃሚነት አድጓል፤ ተጠናክሮም ይቀጥላል። • የሌማት ትሩፋት ከመጋቢት ሥጦታዎች አንዱ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ነው። የምርት አቅርቦትን በማስፋት ለተረጋጋ ግብይት እና ለተመጣጠነ ሥርዓተ-ምግብ ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከት ላይም ይገኛል። ኢኒሼቲቩ ለግብርና ኢንቨስትመንትና ለሀገራዊ የሥርዓተ-ምግብ መሻሻል ጉልኅ ሚና እየተጫወተ ነው። የዋጋ ንረትን በማረጋጋት፣ የምርት ስብጥርን በማሳደግና በዘላቂነት በማቅረብ ረገድም የጎላ ሚና አለው። የግድ ሰፋፊ መሬት መፈለግ ሳያሻ በትንሽ ቦታ ብዙ በማምረት ፍጆታን ከመሸፈን አልፎ ኢኮኖሚን በመደጎም እና የሥራ ዕድል በመፍጠርም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው። • የቱሪስት መዳረሻ ልማት ቅርሶች እንዲጠገኑ፣ አዳዲስ ሎጂዎች እንዲገነቡ፣ በመዳረሻ ስፍራዎች መሠረተ-ልማት እንዲሟላ ያስቻሉ ተግባራት በለውጡ መንግሥት ተከናውነዋል፤ አሁንም ተጠናክሮ የቀጠለ እና ስኬታማ ኢኒሼቲቭ ነው። በዚህ ሂደት ከሐሳብ አመንጭነት ባሻገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የጻፉትን መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ ጭምር ለቅርስ ጥገናና ለቤተ-መጻሕፍት ግንባታ እንዲውል አድርገዋል። በተጨማሪም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት፤ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ ወደ ተግባር አስገብተዋል። በእነዚህ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። አማራጭ የቱሪስት መዳረሻም ሆነዋል። • የተቋማት ግንባታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል መሪል ሐሳብ በተካሄደው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ፤ የተቋማት ግንባታና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ብለዋል። በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ሲሉም አስገንዝበዋል በወቅቱ። ዘመን የማይለውጣቸው ዘላቂ ጠንካራ ሃገራዊ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ብዙ ርቀት መጓዝም ተችሏል። በመሆኑም የመንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲሆኑ በማድረግ እና ሥርዓት በተለዋወጠ ቁጥር የማይፈርሱ ወይም የሚሻገሩ ተቋማት መገንባት ተችሏል። ይህ ትጋት ተጠናክሮም ቀጥሏል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 18, 2026 194
ከሚያዝያ 5 እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ በንፋስ ኃይል አማካኝነት ጨለማን ለመግፈፍ፣ ዐቅምን በለየ የቅድመ ጥናት እና ልዩ ዕቅድ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ዕውን አድርጋለች ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት 100 ሜጋ ዋት ንጹህ የኃይል አቅርቦት በመጨመር ወደ ዘርፈ-ብዙ እና ቀጣይነት ባለው የኃይል መጻዒ ዕጣ ፈንታ ለመገንባት የምናደርገውን ጉዞ ያጠናክረዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ አብነት ነው ብለዋል በወቅቱ። በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል፤ ከምንጊዜውም በላይ ታላቅ የምንሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉም አመላክተዋል። • ከኮፕ32 አስተናጋጅነት ጋር በተያያዘ ምክክር መደረጉ የኮፕ32 አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ መጀመሯን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል ሲሉ ገልጸዋል። ከግምገማ ባሻገር የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልኅቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው ብለዋል። • የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከዚያም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይትም፤ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በቅኝ ያልተገዙ፣ ለአኅጉሩ ነፃነትና አንድነት ድምፅ በመሆን ከጋራ የጽናት ታሪክ የሚመነጭ ጥልቅና ዘመናትን የተሻገረ ግንኙነት አላቸው ያሉት ጠላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም እንደ ሁሌው ኢትዮጵያ ከሰፊ ገበታዋ ያላትን ታላቅ ዐቅምና ዘላቂ ወዳጅነት አብረዋት ለሚጓዙ ሁሉ ለማካፈል ዝግጁ ናት ብለዋል። ጉብኝቱም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን የቆየ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለማስፋት ወሳኝ ምዕራፍን ከፍቷል ሲሉ ገልጸዋል። ከሁለትዮሽ ስብሰባው በመቀጠልም በሁለቱ ሀገራት በኩል ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጉዞ ያካበተችውን ልምድ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማካፈል እንዲሁም ከአጋሮቻችን የተለያዩ ዕይታዎችን በመቅሰም ለአኅጉሩ ዕድገት ዘላቂና አፍሪካዊ መፍትሔዎችን በጋራ ለማፍለቅ እንደ ወሳኝ መሠረት ያገለግላሉ ነው ያሉት። • የፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ባሳለፍነው ሳምንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ቀጣይ ትብብሮችን በምናጠናክርባቸው ቁልፍ መስኮች ላይ መክረናል ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም፤ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ፣ የተሻገረ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ በበቂ ሁኔታ ዜጎችን ሥራ ለማስያዝ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሚና አይተኬ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሥራ ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚ ያሸጋግራል፣ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሻገር እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ያገለግላል በማለት አብራርተዋል። በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነት አንዱ አንጓ ነው በማለት አስረድተዋል። የብዙ መንግሥታትና የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል። አክለውም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል። አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል። እንዲሁም የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግሥት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አብራርተዋል። ከተማ አያስፈልግኝም፤ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አመላክተዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በወሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገራችን በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ሥር እየሰደደ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሐሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል። እንዲሁም በ "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ሥራ ማስጀመራቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ማሳያ እና የወሎ የብልጽግና ተስፋ ነው ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የ"መደመር" ዕሳቤ በተግባር የታየበት፣ የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለ ሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት ነው ሲሉም ገልጸል። ያየነው ልማት የሰላም ውጤት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ በማለት፤ በአንድነት እና በትጋት ከሠራን ይህ ቀጣና የዕድገትና ብልጽግና መዳረሻ መሆኑ አይቀሬ ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንትን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት መሠረተ-ልማት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ግብዓቶችን በማመላለስ የኢኮኖሚያችን የደም ሥር፣ የብልጽግናችን መሠረት ነው ብለዋል። በዐውደ ርዕዩ የተመለከትነውም ወሳኝ የልማት ተቋሞቻችን፣ መሠረተ-ልማትን እንደ ሀገር በቅንጅትና በትብብር የመምራት አዲስ የሥራ ባህል እየገነቡ መሆናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግሥት በመንገድ፣ በኃይል፣ በመስኖ፣ በባቡርና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፍ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚሠራውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። አሁን ያለንበት ወቅት የሥራ፣ የውጤት እና የተስፋ ዘመን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ትናንት የተገነባው ለዛሬ፣ ዛሬ የምንገነባው ደግሞ ለነገው ትውልድ ኩራት እና የብልጽግና ዋስትና ነው ብለዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
የንፋስ ኃይል፤ የኢትዮጵያ የብርሃን አድማስ የአረንጓዴ ልማት ሌላኛው ብስራት!!
Apr 18, 2026 116
በቁምልኝ አያሌው የሰው ልጅ የታዳሽ ኃይል ምንጮችን መጠቀም የጀመረው በጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዘመን እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። ለአብነትም፤ ግብፃውያን ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት ጀልባዎችን በባሕር ላይ ለመንዳት የንፋስ ኃይልን ይጠቀሙ ነበር። በሰባተኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ደግሞ ፋርስ (የአሁኗ ኢራን) የመጀመሪያውን በንፋስ ኃይል የሚሠራ የጥራጥሬ መፍጫ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ ማዋል ጀመረች። ግሪኮችና ሮማውያን የውሃ መንኮራኩሮችን በመጠቀም እህል መፍጨት የሚያስችል ፈጠራን እንዳስጀመሩ የታዳሽ ኃይል የታሪክ ማኅደሮች ይጠቁማሉ። ጥንታዊያን ሕዝቦች የፀሐይ ኃይልን ለብርሃንና ለሙቀት ምንጭነት ከመጠቀም ባለፈ፣ የፀሐይ ጨረርን በማሰባሰብ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚጠቀሙባቸውን ጥበቦች ነበሯቸው። ምንም እንኳን የ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢንዱስትሪ አብዮት በድንጋይ ከሰልና በተፈጥሮ ዘይት የበላይነት ቢያዝም፤ በዚሁ ወቅት ለታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ልማት መሠረት መጣሉን ታሪክ ያስትውሰናል። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው እ.አ.አ በ1839 ፈረንሳዊ የፊዚክስ ሊቅ ኤድመንድ ቤኩረል፤ የፀሐይ ብርሃንን ወደ ኤሌክትሪክ መቀየር የሚቻልበትን የ'ፎቶቮልታይክ' (Photovoltaic effect) ክስተት ማገኘቱ ነው። በተጨማሪም እ.አ.አ በ1882 የመጀመሪያው በውሃ ኃይል የሚሰራ የኤሌክትሪክ ማመንጫ በአሜሪካ ሥራ ጀመረ። እ.አ.አ በ1883 ደግሞ በኦስትሪያ ቪየና በተካሄደው ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ኤግዚቢሽን፣ የንፋስ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ የሚቀይሩ ተርባይኖችን ለመትከል የሚያስችሉ ወሳኝ የቴክኖሎጂ ዕድሎች ታይተዋል። በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ለታዳሽ ኃይል የሚሰጠው ትኩረት መቀዛቀዝ ቢያሳይም፣ በ1970ዎቹ የተከሰተው ዓለም አቀፍ የነዳጅ እጥረት ዓለም አማራጮችን እንድታማትር አስገድዷታል። በዚህም ምክንያት የነዳጅ ዋጋ መናር ሀገራት ከነዳጅ ጥገኝነት ለመውጣት ወደ ውሃ፣ ፀሐይና ንፋስ ኃይል ፊታቸውን እንዲያዞሩና በዘርፉ ለሚካሄድ ጥናትና ምርምር ከፍተኛ መነሳሳት እንዲፈጠር አድርጓል። የንፋስ ኃይል ታሪካዊ ዳራና የቴክኖሎጂ እድገት የንፋስ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ የመቀየር ታሪክ እ.አ.አ በ1883 በኦስትሪያ ቪየና በተካሄደው ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ኤግዚቢሽን ላይ ፍሬድላንድ በተሰኙ ሳይንቲስት አማካኝነት የመጀመሪያው የንፋስ ኤሌክትሪክ ተርባይን ለእይታ መቅረቡ ይነገራል። ይህ የፈጠራ ሥራ በየጊዜው እየተሻሻለ መጥቷል። በ1887 ስኮትላንዳዊው የኮሌጅ ፕሮፌሰር ጄምስ ብሊዝ የቤታቸውን መብራት ለማብራት የተጠቀሙበት የንፋስ ተርባይን በዘርፉ ትልቅ እመርታ ተደርጎ ይወሰዳል። ፕሮፌሰሩ ቀስ በቀስ የፈጠራ ውጤታቸውን አሳድገዋል። የአካባቢው ማኅበረሰብም የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ እንዲሆን ያቸሉትን አድርገዋል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታ በበርካታ ሀገራት የተለያዩ ሙከራዎች መደረጉን ድርሳናት ሲፈተሹ የሚያሳዩት እውነት ነው። ሆኖም ዘርፉ ትኩረት አግኝቶ እንዲያድግ ያደረገው በ1973 በዓለም ላይ የተከሰተው የነዳጅ ቀውስ ነው። ይህ ክስተት ሀገራት ወደ አማራጭ ኃይል ምንጮች እንዲያተኩሩ ዕድል ፈጥሮላቸዋል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ መጠነ ሰፊ የንፋስ ኃይል እርሻዎችን (Wind Farms) በመገንባት ግንባር ቀደም መሆን ችላለች። እ.አ.አ እስከ 2008 ድረስ ከዘርፉ የምታመነጨውን የኃይል መጠን ወደ 24.4 ጊጋ ዋት አሳድጋለች። የንፋስ ኃይል የማመንጨት ሂደት የንፋስን የተፈጥሮ እንቅስቃሴ በተርባይኖች አማካኝነት ወደ ሜካኒካዊ ኃይል፣ በመቀጠልም ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚቀይር ዘመናዊ የታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ነው። ሂደቱም የተርባይን ክንፎች በንፋስ ግፊት አማካኝነት በሚፈጥሩት ሽክርክሪት ጀኔሬተሩን በማንቀሳቀስ ኤሌክትሪክ እንዲመነጭ ያደርጋል። የዓለማችን ግዙፍ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች የት ይገኛሉ? በአሁኑ ወቅት በዓለማችን ከ350 ሺህ በላይ የንፋስ ተርባይኖች ተተክለው ኃይል እየሰጡ ይገኛል። ቻይና በንፋስ ኃይል ማመንጨት የዓለማችን ቀዳሚ ሀገር ስትሆን፤ አሜሪካ እና ጀርመን በቅደም ተከተል ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። የቻይናው ጂኳን (Gansu) የንፋስ ኃይል ማመንጫም ከ20,000 ሜጋ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ያለ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው። የንፋስ ኃይል በኢትዮጵያ ዓለም ለታዳሽ ኃይል ልማት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያም በአፍሪካ የንፋስ ኃይል ልማት ቀዳሚ ተዋናይ የሚያደርጋትን ስራዎች እያከናወነች ነው። ሀገሪቷ በምስራቅ አፍሪካ ያላት ስትራቴጂካዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ የታደለችውን የተፈጥሮ ፀጋ ወደ አማራጭ ኃይል ለመቀየር ሰፊ ዕድል ፈጥሮላታል። በንፋስ ኃይል ልማት የመጣው ከፍተኛ ለውጥም የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፍላጎትን በመሙላት የብዝኅ ታዳሽ ኃይል አማራጭ ልማት እንዲጎለብት እያደረገ ይገኛል። የተፈጥሮ ስጦታና ያልተነካው የኢትዮጵያ እምቅ የንፋስ ኃይል ፀጋ ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አኳያ በንፋስ ኃይል አማራጭ እምቅ የመልማት ፀጋን ተችሯታል። በተለይም የታላቁ ስምጥ ሸለቆ፣ ሰሜናዊ ተራራማ ስፍራዎችና ምስራቃዊ ቆላማ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የንፋስ ፍጥነት ኃይልን ለማመንጨት ተስማሚ መልክዓ ምድሮች ናቸው። በዚህም ኢትዮጵያ እስከ አንድ ነጥብ ሦስት ሚሊዮን ሜጋ ዋት የንፋስ ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይህ አሃዛዊ መረጃም ከአሁኑ ወቅት አጠቃላይ ኃይል የማመንጨት አቅም ጋር ሲነፃጸር ሰፊ የልማት ዕድል መኖሩን ያረጋግጣል። ከጅምር እስከ ዛሬ የስኬት ጉዞ ምዕራፍ የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማት በ2001 ዓ.ም አሸጎዳ ፕሮጀክት ግንባታ ተጀምሯል። በአዳማ 1 እና 2 ስራውን በማስፋት አሁን ላይ እስከ አይሻ 1 እና አሰላ ፕሮጀክቶች ደርሷል። እነዚህ የአዳማ፣ የአሸጎዳ፣ የአይሻ እና የአሰላ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል አድማስ መስፋፋትን የሚያረጋግጡ ናቸው። ለሀገሪቷ አረንጓዴ ልማት ብስራት የሆኑ ታላላቅ ስራዎች ናቸው። አዳማ-1 እና ሁለት፡- በአጠቃላይ 204 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው የአዳማ የኤሌከትሪክ ማመንጫዎች የኢትዮጵያን የንፋስ ኃይል የማመንጨት አቅም በተግባር ያረጋገጡ ፋና ወጊዎች ናቸው። አሸጎዳ፡- በፈረንሳይ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ የተገነባ ሁለተኛው የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ነው። 120 ሜጋ ዋት የሚያመነጨው ይህ ጣቢያ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሚገኙ ዜጎች ከሚሰጠው ብርሃን በተጨማሪ የኢንዱስትሪ አቅም ሆኗል። አይሻ-2፡- በቅርቡ ተመርቆ ወደ ስራ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 80 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል። በኢትዮ-ጅቡቲ ድንበር አቅራቢያ መገናባቱም ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ አለው። አሰላ፡- በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን የምትገኝ የኢትዮጵያ ብርቅየ አትሌቶች መፍለቂያ ስፍራ ናት። በስንዴና ገብስ የግብርና ምርታማነትም በተምሳሌትነት ትጠቀሳለች። ነፋሻማ የአየር ሁኔታዋም ለኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አቅም የሚሆን ፀጋን ተችሯታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ 08 ቀን 2018 ዓ.ም 100 ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚያስችለውን የአሰላ ንፋስ ኃይል መርቀዋል። በዚሁ ወቅትም አርሲ በስንዴና ገብስ ብቻ ሳይሆን በንፋስ ኃይልም የኢትዮጵያ ብልፅግና ማዕከል መሆኗን የአካባቢውን የብዝኅ ፀጋ አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትም ኢትዮጵያ ከዕዳና ኪሳራ ወጥታ ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው ጊዜ ማጠናቀቅና ማትረፍ መጀመሯን በተግባር ያሳየ ነው። ከዚህም በላይ በንፋስ እና በጂኦተርማል ኃይል ማመንጫዎች የኢነርጂ ማዕከል እየሆነ መምጣቷን ያረጋግጣል። "አርሲ በኃይል ዘርፍ ልክ እንደ ስንዴ እና ገብስ ተጨማሪ አቅም ያለው አካባቢ መሆኑን ማየት ችለናል" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በንግግራቸው። የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ በ145 ሚሊዮን ዩሮ ወጪ የተገነባ መሆኑን በመጥቀስ፤ ፕሮጀክቱ በአዋጭነት ደረጃ ሲታይ እጅግ ስኬታማ ነው ብለዋል። ከዚህ ቀደም የሚወሰዱ ብድሮች ለትውልድ ዕዳ ትተው የሚያልፉ እንደነበሩ በማስታወስ፣ የአሁኑን ፕሮጀክት የተለየ የሚያደርገውን ነጥብ ሲያነሱ ይህ ፕሮጀክት ቢበዛ በሁለት ዓመት ሙሉ ወጪውን ሸፍኖ ትርፋማ ስለሚሆን ልጆቻችን ትርፍ ሀብት የሚያገኙ እንጂ ዕዳ የሚረከቡ አይሆኑም በማለት ነው የገለጹት። ፕሮጀክቱ እውን እንዲሆን ግማሹን በእርዳታ እንዲሁም ቀሪውን ከወለድ ነጻ በሆነ ብድር ላቀረበችው የዴንማርክ መንግሥት የላቀ ምስጋና አቅርበዋል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱም ቢበዛ በሁለት ዓመት ሙሉ ወጪውን ሸፍኖ ትርፋማ ስለሚሆን ልጆቻችን ምንዳ እንጂ ዕዳ የሚረከቡ እንደማይሆን አስገንዝበዋል። በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ ላይ በደማቅ ሁኔታ የተመረቀው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት የጀመረችውን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ሌላኛው ታሪካዊ አሻራ ነው። በመደመር መንግስት መፅሐፍ ገፅ 206 ላይ እንደተጠቀሰው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ለማስፋፋት ባለፉት ዓመታት ሰፊ ኢንቨስትመንት ተካሂዷል። ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትም ከፍተኛ ለውጥ አሳይቷል። የታላቁ ሕዳሴ የኃይል ማመንጫን ጨምሮ ሌሎች በጅምር ያሉና በሚገባ አገልግሎት እየሰጡ ያልነበሩ ማመንጫዎችን ወደ መስመር ለማስገባት ተችሏል። በዚህም ሀገራችን ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚያስፈልጋትን የኃይል አቅርቦት በሚገባ መሸፈን ችለናል በማለት ተከትቧል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 504 ሜጋ ዋት ኃይል ብሔራዊ የኃይል ቋትን በመመገብ የኃይል አቅርቦት የጀርባ አጥንት ሆነዋል። በኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ቀደም ሲል የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በመንግስት ብቸኛ ይዞታነት ብቻ ሲካናወኑ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት ግን ይህን አሰራር የሚቀይር የፖሊሲ ማሻሻያ ተደርጓል። ባለሃብቶች በመንግስትና የግል አጋርነት (PPP) ማዕቀፍ የሚሳተፉበት ሰፊ ዕድል ለመፍጠር ተችሏል። ይህም የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ከማበረታታቱም በላይ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የግሉን ዘርፍ በኃይል ልማት ላይ ለማሳተፍ የተወሰዱት የፖሊሲ እርምጃዎች አሁን ላይ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ ጀምረዋል። ለአብነትም፤ በሶማሌ ክልል በመንግስትና በግል አጋርነት የሚገነባው የአይሻ-1 እና 3 የንፋስ ኃይል ፕሮጀክት ከ300 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈን ባለፈ፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለውን የኃይል ትስስር በማጠናከር ለጋራ ዕድገት መፋጠን ጉልህ ፋይዳ አለው። ኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ በመገንባትና የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቀነስ ረገድ የምትከተለው የልማት መንገድ ለሌሎች ሀገራትም ተምሳሌት የሚሆን ነው። የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ከብርሃን ባሻገር የንፋስ ኃይል የኢትዮጵያን የኃይል አቅርቦት በማሟላት ለሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ስትራቴጂክ መሰረት እየጣለ ይገኛል። ለአብነትም በኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ እያበረከተ ያለውን ፋይዳ መጥቀስ ይቻላል። የኢነርጂ ዋስትና እና የኃይል ምንጭ ስብጥር፡- በኢትዮጵያ ከውሃ ኃይል የማመንጨት ተግባር ቀዳሚውን ድርሻ ይይዛል። ይህም በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በሚከሰት የድርቅ አደጋ የኃይል አቅርቦት ተጋላጭነት በማስፋት ተፅዕኖ ያሳድራል። የንፋስ ኃይልም የአቅርቦት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ጉልህ ስትራቴጂክ ፋይዳ አለው። በበጋ ወራት የውሃ መጠን ሲቀንስ የንፋስ ኃይልን በመጠቀም ደግሞ የተፈጥሮ ሚዛንን የጠበቀ አስተማማኝ የኃይል ስብጥር ለመገንባት ጉልህ ፋይዳ ያበረክታል። የኢንዱስትሪ መፋጠንና የሥራ ዕድል፡- የኃይል አቅርቦት ለአስተማማኝ የኢንዱስትሪ ምርታማነት የጀርባ አጥንት ነው። የኢንዱስትሪው ዘርፍ ደግሞ ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ሚና አለው። በተለይም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገነቡ የንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶች የዕውቀትና የምርታማነት ሽግግርን በማፋጠን ረገድ ፋይዳቸው የጎላ ነው። እነዚህ ፕሮጀክቶች በንፋስ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ተከላና ጥገና ወቅት የዜጎችን የምህንድስና ክህሎት በማጎልበት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግሩን በተጨባጭ ያጠናክራሉ። ፋብሪካዎች አስተማማኝ ኃይል እንዲያገኙ በማድረግ የገቢ ምርቶችን የመተካትና የወጪ ንግድ አቅማቸውን በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ። ቀጣናዊ ትስስርና የውጭ ምንዛሬ ግኝት፡- የኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከልነት አቅም የሚያጎለብቱ ከአነስተኛ እስከ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል፤ በመገንባታ ሂደትም ናቸው። የንፋስ ኃይል ልማትም ቀጣናው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን እየደገፈ ይገኛል። ይህም የዕድገት ትስስርን በማፋጠን በየዓመቱ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያበረክታል። የአረንጓዴ አሻራና የአካባቢ ጥበቃ፡- የንፋስ ኃይል ከብክለት የፀዳ ንፁህ የኃይል ምንጭ ነው። ይህም ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት የተቸራትን ዓለም አቀፍ ዕውቅና ለማፅናት በቀላሉ አይታይም። የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ የፋይናንስ ገቢን በማሳደግም ተጨማሪ የታዳሽ ኃይል ልማትን ለማጠናከር ያስቻላል። የገጠሩን ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚነት በማስፋትም የአካባቢና የደን መራቆትን ለመቀነስ ያስቻል። የንፋስ ኃይል ልማት ለኢትዮጵያ ቅንጦት አይደለም፤ ይልቁንስ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ዕድገትን የማፋጠን የህልውና ጉዳይ ነው። ለዚህም የንፋስ ኃይል ፀጋዎችን በማልማት ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የንፁህ ኢኮኖሚ ግንባታ ፋና ወጊነት የሚያረጋግጥ የልማት አቅጣጫ ተተልሞ እየተሰራበት ነው። የኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ልማትም አዲስ ተስፋን የፈነጠቀ የብርሃን አድማስና የአረንጓዴ ልማት ሌላኛው ብስራት እየሆነ ይገኛል።
በፈተናዎች ሁሉ የጸናው የኢትዮጵያና የላይቤሪያ ወዳጅነት
Apr 14, 2026 1170
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያና ላይቤሪያ ዘመናትን የተሻገረ ወዳጅነት አላቸው። ይሄ ወዳጅነት በፈተናዎች ጊዜ ሁሉ ጸንቶ የዘለቀም ነው። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ ውስጥ ብቸኛ ነፃ ሀገራት በመሆናቸው፣ በዓለም አቀፍ መድረኮች (ለምሳሌ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ) የአፍሪካውያን ድምፅ ሆነው በጋራ ይቆሙም ነበር። የሀገራቱ የወዳጅነት እና የትብብር ስምምነትም እ.አ.አ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ የጀመረ ሲሆን፣ በመካከላቸው ያለው ዘላቂ ወዳጅነት እና በዓለም አቀፍ መድረኮች (እንደ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት) በጋራ ለመቆም ቃል የተገባበት ሰነድም ተደርጎ ይወሰዳል። የዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መሠረት የጣሉትም ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ እና ፕሬዝዳንት ዊሊያም ቱብማን ናቸው። እ.ኤ.አ. በ1954 ፕሬዝዳንት ቱብማን ወደ አዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ይፋዊ ግንኙነት እንዲጀመር በር ከፍቷል። ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ እ.አ.አ. 1958 ጉብኝት ወደ ሞንሮቪያ በማድረግ፣ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኙ የነፃነት ንቅናቄዎችን በጋራ ለመደገፍ ተወያይተዋል። እነዚህ ጉብኝቶች የሁለትዮሽ ብቻ ሳይሆኑ አህጉራዊ ፋይዳም ነበራቸው። እ.አ.አ በ1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ሲመሰረት፣ ሁለቱ ሀገራት "የሞንሮቪያ" እና "የካዛብላንካ" ቡድኖችን ልዩነት በውይይት በመፍታት ለአህጉሪቱ አንድነት የጀርባ አጥንት መሆናቸውን አስመስክረዋል። በ1960ዎቹ መጀመሪያ ላይ በ”ሞንሮቪያ ቡድን” እና "የካዛብላንካ ቡድን" መካከል የነበረውን ልዩነት ለማጥበብ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በጋራ በመስራታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሊመሰረት ችሏል። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በችግር ውስጥ የተፈተነ ወዳጅነት ነው የሚል ሀሳብ በብዙዎች ይነሳል። የዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ በላይቤሪያ የነበራት የሰላም ማስከበር ሚና ነው። ላይቤሪያ ለ14 ዓመታት በዘለቀው አውዳሚ የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት መንግሥታዊ መዋቅሯ ፈርሶ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2003 የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ሰላም እንዲያስከብሩ ከጠራቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ ነበረች። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ በርካታ ሰራዊቷን በማሰማራት ለሀገሪቷ ሰላም ዋጋ ከፍላለች። ሰራዊቱ አማፂያንን ትጥቅ በማስፈታት፣ ተዋጊዎች ከማህበረሰብ ጋር እንዲቀላቀሉ በማድረግ እና የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ከፍተኛ ስራ ሰርቷል። ዋና ከተማዋ ሞንሮቪያ እና በገጠራማ አካባቢዎች የተኩስ አቁም ስምምነቱ እንዳይጣስ ጥብቅ ቁጥጥር አድርጓል። የኢትዮጵያ ሰራዊት የጤና ቡድን በየሰፈሩ በመዘዋወር ለላይቤሪያውያን ነፃ የህክምና እርዳታ እና መድሃኒትም ይሰጥ ነበር። ሰራዊቱ የራሱን ስንቅ ለተቸሩ ዜጎች በማካፈል ወንድማማችነትን በተግባር አሳይቷል። እ.ኤ.አ በ2014 የኢቦላ ወረርሽኝ በላይቤሪያ በከፋ ሁኔታ በተከሰተበት ወቅትም፣ ሌሎች ሀገራት ሰራዊታቸውን ሲያስወጡ ኢትዮጵያ ግን የህክምና ቡድኖችን እና ሰራዊቷን በማቆየት ከላይቤሪያ ህዝብ ጎን ቆማች። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ ሶስት ተከታታይ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫዎች እንዲካሄዱ በሰላም ማስከበሩ ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የላይቤሪያ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች የላቀ አገልግሎት ሜዳሊያ እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በላይቤሪያ የነበራት የሰላም ማስከበር ሚና ከወታደራዊ ተልዕኮ ባለፈ የደም እና የአጥንት መስዋዕትነት ከፍላለች። ይህ የሰራዊቱ ተሳትፎ ዛሬም ድረስ በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ላለው ጥብቅ ወዳጅነት ዋነኛው ምክንያት ተደርጎ ይወሳል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራቱ መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች ለሁለትዮሽ ትብብሩ መጠናከር አስተዋጽኦ አድርገዋል። የቀድሞዋ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ እ.አ.አ በ2006 ስልጣን በያዙ ማግስት አዲስ አበባን ጎብኝተዋል። ይህም ኢትዮጵያ በላይቤሪያ ሰላም ለማስፈን ላደረገችው ድጋፍ እውቅና የሰጡበት ነበር። ሰርሊፍ በላይቤሪያ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ሲያበቃ እ.አ.አ ጁላይ 2015 ኢትዮጵያን በመጎብኘት ለተደረገላቸው የህክምና ቡድን ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። የቀድሞዋ ፕሬዝዳንት እ.አ.አ በ2017 ለሶስት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳላኝ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ፕሬዝዳንቷ በወቅቱ የሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክን የጎበኙ ሲሆን ላይቤሪያ ከኢትዮጵያ የጨርቃ ጨርቅ ልማት ዘርፍ ልምድ መቅሰም እንደምትፈልግ በወቅቱ ገልጸው ነበር። የላይቤሪያ የእግር ኳስ ኮከብ እና የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዊሃ እ.አ.አ በ2018 ስልጣን ከያዙ በኋላ በአዲስ አበባ በተካሄደው 30ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የተሳተፉ ሲሆን ከጉባኤው ጎን ለጎን ከወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ተገናኝተው በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ላይ ተወያይተዋል። የቀድሞው የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲ-ማክስዌል ሳህ ከማያህ እ.አ.አ በ2022 በአዲስ አበባ ጉብኝት በማድረግ በሁለቱ ሀገራት መካከል የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን (Joint Ministerial Commission) እንዲቋቋም ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በላይቤሪያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (UNMIL) ላይ በነበረበት ወቅት፣ የተለያዩ የመከላከያ ሚኒስትሮች እና የጦር አዛዦች የኢትዮጵያን ሰላም አስከባሪ ኃይል ለመጎብኘት እና ከላይቤሪያ ባለስልጣናት ጋር ለመወያየት በተደጋጋሚ ወደ ሞንሮቪያ ተጉዘዋል። ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ውይይቶች በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነቶችም ተፈራርመዋል። ሰላም ፣ ደህንነት፣ ጤና፣ የአየር አገልግሎት፣ የቪዛ ነፃ መብት ፣ የንግድ ትብብር ማዕቀፍ፣ ግብርና፣ ትምህርት፣ ባህል እና ስፖርት ስምምነት ከተደረገባቸው ዘርፎች መካከል ይጠቀሳሉ። የአየር አገልግሎት ስምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞንሮቪያ ያለምንም ገደብ እንዲበር እና ላይቤሪያን ከቀሪው ዓለም ጋር ማገናኘት የሚያስችል ህጋዊ ማዕቀፍ ነው። የሰላም ማስከበር ስምምነቱ በተባበሩት መንግሥታት ማዕቀፍ ውስጥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል እንድትልክ የተደረገው ስምምነት በላይቤሪያ መረጋጋት እንዲመጣ ትልቅ ድርሻ ነበረው። በኪነ-ጥበብ እና በስፖርት ዘርፍ (በተለይም በእግር ኳስ) የሁለቱ ሀገራት ወጣቶች ልምድ እንዲለዋወጡ የሚያስችሉ የመግባቢያ ሰነዶች ተፈርመዋል። የወቅቱ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦአከይ እ.አ.አ 2023 ፕሬዝዳንት ሆነው በተመረጡበት ወቅት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ለማደስ እና በንግድ ዘርፍ በጋራ ለመስራት ፍላጎታቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም ከተካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ከላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦአካይ ጋር ውይይት አድርገዋል። የሁለትዮሽ ውይይቱ በቴክኖሎጂ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ኢትዮጵያ ለመገንባት ባቀደችው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ላይ ያተኮረ ነበር። በውይይቶቹ ላይ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በንግድ እና ኢንቨስትመንት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። የላይቤሪያው ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ለስራ ጉብኝት ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክትም የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ የነገ ብሩህ ተስፋ እየተሰራባት ወደ ምትገኘው ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ እንኳን በሰላም መጡ ብለዋል። በፕሬዝዳንቱ ቆይታ እጅግ ፍሬያማ ውይይት እንደሚኖራቸውም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። የፕሬዝዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ የስራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ወዳጅነት የበለጠ እንደሚያጠናክርም ታምኖበታል። የኢትዮጵያ እና የላይቤሪያ መጻኢ ግንኙነት ከታሪካዊ ወዳጅነት ወደ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ አጋርነት የማሳደግ ፍላጎት በሁለቱም ወገን በኩል አለ። በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የአቪዬሽን ትስስር፣ የቴክኖሎጂ ልውውጥ እና በአህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጠና (AfCFTA) ማዕቀፍ የሚደረግ ትብብር ለጋራ ብልጽግና መሰረት ይጥላል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 11, 2026 181
ከመጋቢት 27 እስከ ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦ • ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ የትንሣኤ በዓል በክርስቲያኖች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው በዓል ነው፤ ሞት የተሻረበትና ሕይወት ዋስትና ያገኘበት ነው ብለዋል። የትንሣኤ በዓል ከሞት ባሻገር ሕይወት ከመቃብር ባሻገር ትንሣኤ መኖሩ የታወጀበት መሆኑንም ገልፀው፤ ሞት መጨረሻ መቃብር መዳረሻ አለመሆናቸው የተረጋገጠበት ነው ብለዋል በመልዕክታቸው። የዘንድሮውን ትንሣኤ የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በሚያልፍ ፈተና ውስጥ እንዳለች እያሰብን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን ሲሉ ገልፀዋል። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ በጥልቁ ጨለማ ጠፍተን እንድንቀር አሥረው ለመያዝ የሚሞክሩ ወጥመዶች ብዙ ናቸው፤ ወደ ተስፋ ምድር እንዳንሻገር የሚጎትቱ ሰበቦች ሞልተዋል፤ ዳሩ ግን ከሕማማቱ ወዲያ ትንሣኤ ከዕንቅፋቱ ባሻገር ስኬት እንደሚጠብቀን አምነን እንታገላለን ሲሉም አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ትንሣኤ መቃረቧን ገልፀው፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ከሚበሰርባቸው ምዕራፎች አንዱ ግንቦት ላይ የሚካሄደው ምርጫ መሆኑንም አመላክተዋል። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም ብለዋል። • የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሁለት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ካደረጉት የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት ኢቫሪስቴ ንድያይሺሚዬ ጋር ውጤታማ የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን ባሳለፍነው ሳምንት ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ለማጠናከር ያለሙ በርካታ የመግባቢያ ሰነዶች ፊርማ አከናውነናል ሲሉም አስታውቀዋል። ስምምነቶቹ ለሁለቱም ሀገራት የበለጸገ እና የተባበረ መጻኢ ዕድልን የሚያረጋግጡ የቆዩ ግንኙነቶቻችንን ወደ ተጨባጭ ትብብር ለመቀየር እንደ ወሳኝ መሠረት የሚያገለግሉ የጋራ ቁርጠኝነታችን ማሳያ ጭምር ናቸው ብለዋል። ጉብኝታቸውን እንዳጠናቀቁም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው ሸኝተዋቸዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪኤግዚም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኢሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም ስትራቴጂካዊ ግንኙነታችንን በምናጠናክርባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረናል ብለዋል። • የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሥተዳደር ዓመታዊ አፈጻጸም ግምገማ ባሳላፍነው ማክሰኞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሥተዳደር ፕሬዚዳንት ሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦላቸው በውጤቶቹ ላይ ግምገማ እና ውይይት አድርገዋል። • የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ሹመት መራዘም በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 62(9) እና በዐዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀፅ 2(ለ) መሠረት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አሥተዳደርን በርዕሰ መሥተዳደርነት እንዲመሩ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አሥተዳደር አስመልክቶ በጸደቀው ደንብ ቁጥር 479/2013 አንቀጽ 4(2) እና የዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ባቀረቡት መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደን ሹመት ለአንድ ዓመት አራዝመዋል። • ማዕድ ማጋራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች እና ጽሕፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሕጻናት ማዕድ አጋርተዋል። • የአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ኅልፈተ ሕይወት አምባሳደር ቆንጅት፤ በዲፕሎማሲው መስክ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ላበረከቱት ጉልኅ አስተዋጽዖ፣ ለሰጡት አስተምኅሮና ለነበራቸው ብልኅ አመራር ምንጊዜም ሲታወሱ እንደሚኖሩ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባስተላለፉት የኀዘን መግለጫ መልዕክት ገልጸዋል። ትጉኅና ከብረት የጠነከሩ ዲፕሎማት ነበሩ በማለት ለሙያቸው የነበራቸውን ጽኑ አቋምና የሀገር ፍቅር ስሜትም አንስተዋል። ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት በማረፋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሰማቸውን ኀዘን ገልጸዋል። አምባሳደሯ ለሕግ፣ ለአሠራር፣ ለፕሮቶኮል እና ለኢትዮጵያ ጥቅሞች በነበራቸው የጸና አቋም እናስታውሳቸዋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከእርሳቸው በኋላ አያሌ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል ብለዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባስተላለፉት የኀዘን መግለጫ መልዕክት፤ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ እና ታላቅ ዐሻራን ማሳረፍ የቻሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ጥልቅ ኀዘን ተሰምቶኛል ብለዋል። አምባሳደር ቆንጂት እስከ ከፍተኛ ዲፕሎማትነት በደረሰ ረጅም የሥራ ዘመናቸው ለሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ያስመዘገቡት ድል እና ያበረከቱት አስተዋጽዖ ሁልጊዜም በክብር የሚታወስ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ባሳለፍነው ሳምንት “ፖሊሳዊ አንድነት ለዘላቂ ሰላም” በሚል መሪ ሐሳብ 20ኛው የፖሊስ ኮሚሽነሮች መክፈቻ ጉባዔ ተካሂዷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፤ የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያ ፖሊስ በሚሰጠው አገልግሎት ታማኝም አሳማኝም መሆን አለበት ብሎ ያምናል ብለዋል። የፖሊስ ኃይላችን የጥፋት ኃይሎች በሀገራችንና በሕዝባችን ላይ የሰነዘሩትን ጥቃት በአንድነት በመቆምና መስዋዕትነት በመክፈል ቀልብሷል፤ ይህም ለሁላችንም ኩራት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የፖሊስ አመራሮችና የሠራዊቱ አባላት በዕውቀት፣ በታማኝነትና በሕዝብ አገልጋይነት ሥነ-ልቦና ለላቀ ተልዕኮ እንድትዘጋጁ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3893
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2652
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8443
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6931
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 491
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ
Apr 12, 2026 982
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ በቀበኔሳ ገቢሳ ትንሣኤ ለሰው ልጅ ተስፋን፣ ዘለዓለማዊ ሕይወትን እና ከኃጢአት ነፃ መውጣትን የሚያበስር ኃይማኖታዊ በዓል ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ በመነሳቱ የሰው ልጅ የዘለዓለም የሕይወት አክሊልን ተስፋ ያደረገበት፣ የእግዚአብሔር ፍቅር የተገለጠበት እንዲሁም የሰው ልጅ ከዘለዓለም ሞትና ከኃጢአት ባርነት ነፃ የወጣበት የድኅነት፣ የፍቅር፣ የጽናትና የተስፋ ብርሃን ብስራት ነው፡፡ የትንሣኤ በዓል ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የመነሳቱ ታላቅ ምሥጢር የሚታሰብበት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንስ የሰው ልጅ ከውርደት ወደ ክብር፣ ከኃጢያት ባርነት ወደ ድኅነት እንዲሁም ከጉስቁልና ወደ ብሩህ ተስፋ የተሸጋገረበት የድል አዋጅ ነው። በዕለቱም በሞት ላይ ሕይወት፣ በሐዘን ላይ ደስታ፣ በቂም ላይ ይቅርታ ተበስሮበታል። ከበዓላት ሁሉ የላቀ የነጻነት ተምሳሌት ነው ትንሣኤ። 👉የትንሣኤ ሕያው አስተምሮ በዕለት ተዕለት ሕይወት ትንሣኤ ሲከበር ከሥርዓተ አምልኮ ባለፈ፣ በዓሉ የሚሰጠውን ታላቅ አስተምሮ ማጤን ይገባል። ትንሣኤ በየቀኑ ካለንበት ድካምና ውድቀት በአዲስ መንፈስ የመነሳት አቅም ነው። በዓሉ የሚያስተምረንን የጽናት፣ የተስፋና የአብሮነት ዕሴት በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ መኖር ያስፈልጋል። ለዚህም የተቸገሩን መርዳት፣ የታመሙትን መጠየቅና የተጣሉትን ማስታረቅ የበዓሉን ትርጉም እውነተኛ ያደርገዋል። 👉የኢትዮጵያ ትንሣኤ፤ በፈተና የጸና ብርሃን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዓሉን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት፤ "የዘንድሮውን የትንሣኤ በዓል የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በፈታኝ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ሆና እያለች ነው። መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችንም እሾህ የበዛበት ሊሆን ይችላል። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ፣ በጨለማ ወጥመድ ሊያሥሩን የሚሞክሩ መሰናክሎች ቢበዙም፣ እምነታችን ግን ከሕማማት በኋላ ትንሣኤ እንደሚመጣ ነው" ብለዋል፡፡ "ኢትዮጵያ ዛሬም ትንሳኤዋን እያየች ነው። መቃብሯ ተከፍቷል፤ ማኅተሙም ተሰብሯል። የትንሣኤውን ዜና ሊያደበዝዙ የሚሞክሩ የውሸት ወሬዎችና ተስፋ አስቆራጭ ትረካዎች የሀገራችንን የብርሃን ጉዞ ሊገቱት አይችሉም። ትንሳኤው እውነት ነው፤ ብርሃኑም የማይቀለበስ ሀቅ ሆኗል" ሲሉም አረጋግጠዋል፡፡ 👉ዴሞክራሲ እና ብሔራዊ ምክክር፤ የተስፋ ምዕራፎች የኢትዮጵያ ትንሣኤ አንዱ መገለጫ ዴሞክራሲን የመገንባት ጽናት ነው። ትንሣኤ ያለ ሕማማት እንደማይገኝ ሁሉ ዴሞክራሲ ያለ ፈተና በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ዴሞክራሲ የሚገነባው በጽናት እንጂ በፍርሃት አይደለም። ዴሞክራሲን እየገነባን በትዕግሥትና በቆራጥነት ወደ ተስፋዋ ምድር እንደርሳለን። አሁን ያለው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጦርነት፣ የኢኮኖሚ ቀውስና ማህበራዊ አለመረጋጋት የትንሳኤን ትምህርት ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊ ያደርገዋል፡፡ ችግሮችን በብቸኝነት የምንወጣበት ጊዜ አብቅቷል። ዛሬ እንደህዝብ የሚያስፈልገን ከ"እኔ" ወደ "እኛ" መሸጋገር፣ የግል ፍላጎትን ለጋራ ስኬት መስዋዕት ማድረግ ግድ የሚልበት ወቅት ላይ ነን። የአንድነት ጉዟችንን በማጠናከር ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ጫናዎችን ለመቋቋም በጋራ መቆም ይገባናል። የተቸገሩትን በመርዳት፣ የታመሙትን በመጠየቅና የተጣሉትን በማስታረቅ የተግባር አብሮነትን በማሳየት የበዓሉን እውነተኛ ትርጉም መግለጥ ይገባል፡፡ 👉ምርጫ፤ ከኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበትና ተስፋ የታደሰበት ዕለት ነው። እኛም በምርጫ ካርዳችን የሃሳብ ልዩነትን በዴሞክራሲያዊ አንድነት ድል በማድረግ የኢትዮጵያን የብልፅግና ትንሳኤ እናረጋግጣለን። በትንሣኤ በዓል የምንማረው ይቅርታና ጽናትም ለምርጫችን ስኬት አቅም ይሆናል። በኅብረት የምንሰጠው ድምፅም የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ የመቅረጽ ኃይል በእጃችን መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው "ምርጫ የኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ነው። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም። በዓለም ላይ በደልዳላ መንገድ ተጉዞ ዴሞክራሲን የገነባ ሀገር የለም። ዴሞክራሲና ብልፅግና ያለ ጽናት አይሳኩም። ከእኛ በፊት ዐመጻውን በትዕግሥት የመከቱ ተሻግረዋል፤ ሑካታውን በጽናት ያለፉ አሳክተዋል። ብንመኝም ፈተናውን አናስቀርም፤ መጽናት ግን እንችላለን። ከድኅነት መውጫው ብርታታችን፣ ወደ ዴሞክራሲ መድረሻችው ትዕግሥታችን እንደሆነ አምነን ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በሙሉ ልባችን እንትጋ!!" ብለዋል። 👉የወደፊት እጣ ፈንታችን በእጃችን ከፊታችን የሚጠብቁን ሀገራዊ ምክክርና የ2018 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የወደፊት መጻኢ ዕድል የሚወስኑ ታላላቅ ሁነቶች ናቸው። እነዚህ ሂደቶች ስኬታማ የሚሆኑት እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን ሲወጣ ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በልባችን ውስጥ ይቅርታና አብሮነት ሲነግስ ብቻ ግቡን ይመታል። ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበት እንደሆነው ሁሉ፣ በምክክሩም ጥልን፣ ጥርጣሬን፣ ያለመግባባት መንፈስን ድል መንሳት ይገባል፤ ቅንነት፣ ተስፋና መተሳሰብ ለምክክሩ ስኬት የመተማመኛ ቁልፎች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ 2018 ዓ.ም ደግሞ የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ ማሳያ አንጓ ነው፤ የዜጎች ነፃ ተሳትፎ መብታቸውን የሚያስከብሩበት ፍላጎታቸውን የሚያረጋግጡበት ማረጋገጫ ማህተም ጭምር፡፡ ዜጎች የመምረጥና የመመረጥ መብታቸውን የሚያስከብሩበት፤ የሌላውን ሃሳብ አክብረው የራሳቸውን የሚያስከብሩበት ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በጋራ የሚቆሙበት መድረክ ነው፡፡ ትንሣኤ የድልና የነጻነት በዓል ነው። ይህንን ታላቅ ዕለት ስናከብር ያለፈውን ቁስል ሽረን፣ ለነገ ተስፋ ሰንቀን መሆን አለበት። እርስ በእርስ በመደጋገፍ፣ ችግሮችን በንግግር በመፍታት ለሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ስኬታማነት የድርሻችንን መወጣት ይገባናል። የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ እንቁም! መልካም የትንሳኤ በዓል!!