ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረግን ነው
Apr 4, 2026 28
ጅማ ፤መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም በማስቀደም በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረጉ መሆኑን የተለያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ ሃላፊዎች ተናገሩ። የለውጡ መንግስት ባለፉት ዓመታት በዲፕሎማሲ፣ በፖለቲካ፣ ማህበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ ዘርፎች ስኬቶችን በተግባር ያረጋገጠበት ስኬታማ አመት መሆኑን በብዙ ማሳየዎች መግለጽ ይቻላል። የተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ ሰላማዊ ትግል እያደረጉ እና የመንግስት ተቋማትን የመምራት እድል የተሰጣቸው መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም በማስቀደም በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረጉ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች ገልጸዋል። የሸካ ዞን የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ሀይሉ ተስፋዬ፤ ከለውጡ በፊት በፖለቲካው ለመሳተፍ ባደረጉት ጥረት በጠላትነት ተፈርጀውና ተገፍተው መቆየታቸውን አስታውሰው በለውጡ በተፈጠረው ምቹ ምህዳር በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርም በሀገር ብሄራዊ ጥቅም እና የዜጎች ክብር ላይ የጋራ አቋም ያላቸው መሆኑን አንስተው ከማይገባ ተቃርኖ እና የጠላትነት እሳቤ በመውጣት በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረግን ለዘንድሮውም ጠቅላላ ምርጫ ዝግጅት እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) አስተባባሪ አቶ ሰለሞን መኮንን፤ ለውጡ በተለይም የፖለቲካውን ምህዳር በማስፋት እና አሳታፊ በማድረግ የሚታይና ተጨባጭ ውጤት የመጣበት ሆኗል ብለዋል። በፖለቲካ ፉክክሩ በሀገር ብሄራዊ ጥቅም ላይ የጋራ አቋም መኖሩን አንስተው ከገዢው ፓርቲ ጋር ስለ ሀገር እና የዜጎች ጉዳይ ላይ ተቀራርበን እየሰራን እንገኛለን ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ እያደገ እንዲመጣ ኢዜማ የበኩሉን መወጣቱን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደንበኞችን እርካታ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አሰራሮችን እየተገበረ ነው
Apr 4, 2026 46
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ግልጽነትንና ተጠያቂነትን በማስፈን የደንበኞችን እርካታ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አሰራሮችን እየተገበረ እንደሚገኝ ገለጸ። መንግሥት የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እንዲሰጡ የሪፎርም ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም እንደ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያሉ በአጭር ጊዜ የህዝብን የእርካታ መጠን ማረጋገጥ የቻሉ ተቋማትን መገንባት ተችሏል። ይህን መሰረት በማድረግ ሌሎች የመንግሥት ተቋማትም አሰራራቸውን በማዘመንና ከህዝብ ጋር በመቀራረብ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የሚያስችል ስልት እየተከተሉ ይገኛል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ዳይሬክተር ህብረወርቅ ይመኑ፣ ተቋሙ የደንበኞችን እርካታ ለማሳደግ የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ደንበኞች በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚገጥሟቸውን ብልሹ አሰራሮችን በምስጢር መጠቆም የሚችሉበትን ቀላል፣ ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀ መተግበሪያ ስራ ላይ ማዋሉን አስታውቀዋል። በዚህም ደንበኞች "eeuethics.et" በተሰኘው ድረ-ገጽ በመግባት ወይም መተግበሪያውን ስልካቸው ላይ በመጫን ቅሬታቸውንና ጥቆማቸውን በቀላሉ ማቅረብ እንደሚችሉ ገልጸዋል። መተግበሪያው የደንበኞችን የጥቆማ ተሳትፎ ማሳደግ የቻለ ሲሆን፣ ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ 374 ጥቆማዎች መቅረባቸውን አብራርተዋል። ከጥቆማዎች መካከል በማጣራትም በተገኙ ግኝቶች መሠረት በ98 ሰራተኞች ላይ ህጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። ተቋሙ ለጠቋሚዎች ተገቢውን ጥበቃ በማድረግ ብልሹ አሰራሮችን በድፍረት እንዲያጋልጡ የሚያስችል የእውቅና አሰጣጥና የጥበቃ መመሪያ አዘጋጅቶ ወደ ሥራ ማስገባቱንም ገልጸዋል። የአሰራር ስርዓትን በቴክኖሎጂ ከማዘመን ባለፈም የሰራተኞችን የስነ-ምግባር ሁኔታ ለመለየት የሚያስችል ልዩ ማዕቀፍ መዘጋጀቱን አስረድተዋል። ደንበኞች ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉና ለማንኛውም አገልግሎት ክፍያ ሲፈጽሙ ህጋዊ ደረሰኝ የመቀበል ግዴታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
ለግብርና ትራንስፎርሜሽንና ሜካናይዜሽን የተሰጠው ትኩረት ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ መሰረት እየጣለ ነው
Apr 4, 2026 90
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለግብርና ትራንስፎርሜሽንና ሜካናይዜሽን የሰጠችው ትኩረት ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ መሰረት እየጣለ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ። የ2018/19 የሰብል ልማት ንቅናቄ "በምርትና ምርታማነት የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው። የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ መፃኢ ጊዜ የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ አኳያ ብሩህ ነው። በመደመር መንግሥት የተጀመረው የግብርና ትራንስፎርሜሽን እንቅስቃሴ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ በተጨባጭ ውጤት መታየት መጀመሩን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ግብርና ዘመናዊ በማድረግ ወደ ሜካናይዜሽን እየተሸጋገረ መምጣቱን ገልጸው፤ በኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው ተግባር ተጨባጭ ለውጥ መታየቱን ተናግረዋል። የ2018/19 የመኸርና የበጋ ሰብል ልማት ወቅት በዓለም አቀፍ ቀውስ ፈተና ውስጥ ሆና የሚካሄድ መሆኑን ገልጸው፤ ነገር ግን የአፈር ማዳበሪያ ቀድሞ በማስገባት ስጋቱን መሻገር መቻሉን ገልጸዋል። በተለይም የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት የሎጂስቲክ ስርዓቱን ላይ የሚያደርሰውን ጫና ለመቋቋም ሌት ተቀን በትጋት መሥራት ይገባናል ብለዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየርንበትን ልምድ ዛሬም ማስቀጠል ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ጌቱ ገመቹ በበኩላቸው፤ በክልሉ ከ33 በላይ ኢኒሼቲቭ ተግባራዊ ተደርጓል ብለዋል። ክልሎች ያላቸውን የተፈጥሮ ጸጋ በአግባቡ በመተግበር በትጋት መስራት ከተቻለ ለውጥ እንደሚመጣ ኢንሼቲቮች በተግባር ማሳየታቸውን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች ያሉ ልምዶችን በመውሰድ ዝርያዎችን በማላመድ ዓይነት ብዙ ምርቶችን ማምረት መጀመሩን ገልጸው፤ ከአማራ ክልል ልምድ በመቅሰም ሩዝ ማምረት መቻሉን ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚመልሱ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Apr 4, 2026 61
ጅማ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለህዝቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ ገለጹ። በጅማ ዞን ኦሞ ናዳ ወረዳ አሰንዳቦ ከተማ፣ በወረዳ ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። አቶ ነመራ ቡሊ በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሉ በስፋት እየተተገበረ መሆኑንና የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በሂደት ለመመለስ እየተከናወነ ያለ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። አገልግሎቱ ብልሹ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ፣ የህዝቡን ጥያቄዎች አንድ በአንድ እየመለስን ለመሆናችን ማሳያ ነው ያሉት ኃላፊው፣ ወደፊትም አገልግሎቱን በማዘመን ለበርካታ ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የጅማ ዞን አስተዳዳሪ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፣ የዞኑ ነዋሪዎች በተደጋጋሚ የሚያነሷቸውን የልማትና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥያቄዎችን ለመፍታት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በወረዳ ደረጃ እየተስፋፋ መሆኑን ገልጸዋል። የአሰንዳቦ ከተማ አስተዳዳሪ ነዚፍ ሼህ ከማል በማዕከሉ 11 ተቋማት 52 ዓይነት አገልግሎቶች በ8 መስኮቶች እንደሚሰጥ ጠቅሰው ባለሙያዎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ስልጠና ወስደው ወደ ስራ ገብተዋል ብለዋል።
የምርጫ ካርድ በመውሰድ ይጠቅመናል ብለን የምናምንበትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል- የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች
Apr 4, 2026 150
ጅግጅጋ፣መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ የምርጫ ካርድ በመውሰድ ይጠቅመናል ብለን የምናምንበትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን ተወስኖ፣ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ስም እንዲሁም የመለያ ምልክት አደራደር ቅደም ተከተል ለመወሰን የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት አካሒዷል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም ፖሊሲና ስትራቴጂያቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የምርጫ ክርክርና የቅስቀሳ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የኢዜአ ሪፖርተር በየምርጫ ጣቢያዎቹ ተዘዋውሮ የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ያሉ ዜጎችን አነጋግሯል። ከየምርጫ ጣቢያዎቹ አስተያየት የሰጡ ነዋሪዎችም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በምርጫው እለት በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ አብዱላሂ ሀሰን እና አቶ ሙክታር ከድር፤ የምርጫ ሂደት የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የሚረጋገጥበት መሆኑን በማንሳት በእለቱ ለሚፈልጉት ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ካርድ ከመያዝ በተጓዳኝ ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት ሁላችንም የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናልም ብለዋል። ሌላኛው የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኘናቸው አቶ መታን አብዲራህማን፤ የዘንድሮው የምርጫ ሂደት እስካሁን የተቀላጠፈ እና ዘመናዊ አገልገሎት የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በምርጫው እለት ድምፃቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የመራጮች የምዝገባ ሂደት እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከናወን መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ያወጣው የጊዜ ሰሌዳ ያመለክታል።
ፖለቲካ
ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረግን ነው
Apr 4, 2026 28
ጅማ ፤መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም በማስቀደም በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረጉ መሆኑን የተለያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ ሃላፊዎች ተናገሩ። የለውጡ መንግስት ባለፉት ዓመታት በዲፕሎማሲ፣ በፖለቲካ፣ ማህበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ ዘርፎች ስኬቶችን በተግባር ያረጋገጠበት ስኬታማ አመት መሆኑን በብዙ ማሳየዎች መግለጽ ይቻላል። የተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ ሰላማዊ ትግል እያደረጉ እና የመንግስት ተቋማትን የመምራት እድል የተሰጣቸው መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም በማስቀደም በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረጉ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች ገልጸዋል። የሸካ ዞን የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ሀይሉ ተስፋዬ፤ ከለውጡ በፊት በፖለቲካው ለመሳተፍ ባደረጉት ጥረት በጠላትነት ተፈርጀውና ተገፍተው መቆየታቸውን አስታውሰው በለውጡ በተፈጠረው ምቹ ምህዳር በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርም በሀገር ብሄራዊ ጥቅም እና የዜጎች ክብር ላይ የጋራ አቋም ያላቸው መሆኑን አንስተው ከማይገባ ተቃርኖ እና የጠላትነት እሳቤ በመውጣት በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረግን ለዘንድሮውም ጠቅላላ ምርጫ ዝግጅት እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) አስተባባሪ አቶ ሰለሞን መኮንን፤ ለውጡ በተለይም የፖለቲካውን ምህዳር በማስፋት እና አሳታፊ በማድረግ የሚታይና ተጨባጭ ውጤት የመጣበት ሆኗል ብለዋል። በፖለቲካ ፉክክሩ በሀገር ብሄራዊ ጥቅም ላይ የጋራ አቋም መኖሩን አንስተው ከገዢው ፓርቲ ጋር ስለ ሀገር እና የዜጎች ጉዳይ ላይ ተቀራርበን እየሰራን እንገኛለን ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ እያደገ እንዲመጣ ኢዜማ የበኩሉን መወጣቱን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የምርጫ ካርድ በመውሰድ ይጠቅመናል ብለን የምናምንበትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል- የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች
Apr 4, 2026 150
ጅግጅጋ፣መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ የምርጫ ካርድ በመውሰድ ይጠቅመናል ብለን የምናምንበትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን ተወስኖ፣ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ስም እንዲሁም የመለያ ምልክት አደራደር ቅደም ተከተል ለመወሰን የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት አካሒዷል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም ፖሊሲና ስትራቴጂያቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የምርጫ ክርክርና የቅስቀሳ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የኢዜአ ሪፖርተር በየምርጫ ጣቢያዎቹ ተዘዋውሮ የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ያሉ ዜጎችን አነጋግሯል። ከየምርጫ ጣቢያዎቹ አስተያየት የሰጡ ነዋሪዎችም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በምርጫው እለት በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ አብዱላሂ ሀሰን እና አቶ ሙክታር ከድር፤ የምርጫ ሂደት የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የሚረጋገጥበት መሆኑን በማንሳት በእለቱ ለሚፈልጉት ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ካርድ ከመያዝ በተጓዳኝ ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት ሁላችንም የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናልም ብለዋል። ሌላኛው የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኘናቸው አቶ መታን አብዲራህማን፤ የዘንድሮው የምርጫ ሂደት እስካሁን የተቀላጠፈ እና ዘመናዊ አገልገሎት የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በምርጫው እለት ድምፃቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የመራጮች የምዝገባ ሂደት እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከናወን መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ያወጣው የጊዜ ሰሌዳ ያመለክታል።
በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ተዘጋጅተናል- የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች
Apr 3, 2026 1193
ጋምቤላ ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ዘንድሮ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ሲወስዱ ያገኘናቸው የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በንቃት ለመሳተፍ ተዘጋጅተዋል፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡን የከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ኮንግ ቾል እንዳሉት ዘንድሮ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን ካርድ በወቅቱ ወስደዋል፡፡ ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ መያዛቸው የምርጫው ጊዜ ሲደርስ የሚፈልጉትንና ለሀገር የሚበጀውን ሀሳብ የያዘውን ፓርቲንም ሆነ እጩ ለመምረጥ መብት እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል፡፡ የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በጥንቃቄ በመያዝ ለሀገር ይጠቅማል ብለው ለሚያምኑት እጩ ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ አኙት ኡቹዶ ናቸው፡፡ አቶ አብዱ አቡበክር በበኩላቸው፤ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ጊዜው ከማለፉ በፊት መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ የመራጭነት ካርድ መውሰድ የዜግነት ሃላፊነትን ከመወጣት ባለፈ በሀገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት ለሚደረገው ጥረት አይነተኛ ፋይዳ እንዳለውም አብራርተዋል፡፡ ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ሀገራዊ ለውጡ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት በተደመረ አቅም ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ አስችሏል-የፀጥታና ደኅንነት ከፍተኛ አመራሮች
Apr 3, 2026 907
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተቋማት የተደረገው ሪፎርም ጠንካራ የፀጥታና ደህንነት ተቋማት በመፍጠር በተደመረ አቅም ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ ማስቻሉን የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ። ሀገራዊ፣ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የፀጥታና ደኅንነት ምህዳሩን የገመገመው ብሔራዊ የደኅንነት ኮንፈረንስ ተካሂዷል። በኮንፈረንሱ የተሳተፉ የፀጥታና ደኅንነት ከፍተኛ አመራሮች በሰጡት ማብራሪያ ተለዋዋጭ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ ያደረገ ሀገራዊ የፀጥታ ምህዳር መገንባቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንዳሉት፥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት መንግሥት ከተገበራቸው የሪፎርም አምዶች አንዱ ጠንካራና ገለልተኛ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት መገንባት ነው። በሪፎርሙም ፌዴራል ፖሊስን ጨምሮ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት በሰው ኃይል፣በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በአደረጃጀት የላቁ እንዲሆኑ መደረጋቸውን ተናግረዋል። የለውጥ እርምጃዎች በሀገሪቱ ያለውን ፀጥታና ሰላም ለማፅናትና በቀጣይም ተልዕኮዎችን ለመሸከም የሚያስችል ተቋማዊ አቅም መፍጠር ያስቻሉ መሆኑንም ተናግረዋል። ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገራት ጭምር አለኝታ የሆኑ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት መገንባታቸውንም አብራርተዋል። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላ በበኩላቸው፥ ሀገራዊ የፀጥታ፣የመረጃና የደኅንነት ምህዳሩ በተቀናጀ አግባብ በስኬታማነት እየተመራ መሆኑን ተናግረዋል። በሪፎርሙ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ከተከፋፈለ አስተሳሰብ ወጥተው በተደመረ አቅም ሀገራዊ ደህንነትን ማረጋገጥ የሚያስችል የላቀ ብቃት ፈጥረዋል ነው ያሉት። የዘርፉ ሪፎርም ቀጣይነት ባለው መልኩ እየተካሄደ መሆኑንና በተለይ ባለፉት አምስት ዓመታት ከፍታ ላይ መድረሱን ተናግረዋል። የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት የተለያዩ ፈተናዎችን በውጤታማነት በማለፍ እየተጠናከሩ መምጣታቸውንም ገልፀዋል። ተቋማቱ ሀገራዊ፣ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ተልዕኳቸውን በአስተማማኝ ሁኔታ በመወጣት ላይ እንደሚገኙ አንስተዋል። የኦሮሚያ አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ፥ ሀገራዊ ለውጡ በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት መካከል ቅንጅታዊ አሠራርን ያጠናከረ ምህዳር መፍጠሩን ተናግረዋል። በክልል ደረጃም የነበሩ የፀጥታ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱና የሕግ የበላይነት በማስፈን ረገድ ከፍተኛ አቅምና ውጤት ያመጣ ነው ብለዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግሥቴ (ዶ/ር) ተቋማዊ ሪፎርሙ ሀገሪቱ ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚገጥማትን የፀጥታና ደኅንነት ጥቃት በብቃት ለመመከት የሚያስችል አቅም መፍጠሩን ተናግረዋል። የፀጥታና ደኅንነት ሪፎርሙ ተናባቢና ተደጋጋፊ ተቋማትን መፍጠር ያስቻለ መሆኑንም ነው የገለፁት። የፀጥታና ደኅንነት አመራሮቹ አክለውም ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የፀጥታና የደኅንነት ግብረ ኃይል እቅድ በማዘጋጀት እየሠሩ መሆኑን ገልፀዋል። በሀገሪቱ አስተማማኝ ሰላምና ደኅንነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት የተከናወኑ ተግባራት ምርጫውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የሚያስችል አቅምና ዕድል መፍጠራቸውን አስረድተዋል። ከስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተሞክሮ በመነሳት፥ባለፉት ስምንት ወራት የፀጥታ መዋቅሩ የጋራ እቅድ አዘጋጅቶ ከፌዴራል እስከ ክልል ድረስ በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን ጠቅሰዋል። በዚህም ምርጫውን በተሳካ መንገድ ለማካሄድ ምቹ የፀጥታና ደኅንነት ምኅዳር መፈጠሩን ተናግረዋል። ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ ምንም ዓይነት ስጋት እንዳይፈጠር ተቋማቱ ቅንጅታቸውን አጠናክረው እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።
የትግራይ ክልል የመጀመሪያ ዙር የባለድርሻ አካላት የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ ስኬታማ ነው- ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Apr 3, 2026 729
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል የመጀመሪያው ዙር የባለድርሻ አካላት የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ ስኬታማ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የመጀመሪያ ዙር ከመጋቢት 23 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲያካሂድ ቆይቷል። በመጀመሪያው ዙር የተሳተፉ የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት ያጠናቀሩትን አጀንዳ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፈሰር መስፍን አርዓያ በዚሁ ወቅት፥ የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረኩ በሁሉም አካባቢዎች በተደረጉ ስነ-ዘዴዎች መካሄዱን ገልጸዋል። መድረኩ ስኬታማ መሆኑን ጠቁመው፤ ለመድረኩ ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም በበኩላቸው፤ በመድረኩ ከ700 በላይ ተሳታፊዎች የታደሙ ሲሆን በርካታ ሀሳቦች መንሸራሸራቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)፥ የትግራይ ክልል የባለድርሻ አካላት የመጀመሪያው ዙር የአጀንዳ ማሰባሰብ በስኬት መጠናቀቁን ጠቅሰው፥ በቀጣይም የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ እንደሚኖር ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስከበር በሁሉም መስክ ልቆ መገኘትና ትብብርን ማጠናከር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው
Apr 3, 2026 592
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያንና የቀጣናውን ደኅንነትና ጥቅም ለማስከበር በሁሉም መስክ ልቆ መገኘትና ትብብርን ማጠናከር ወቅታዊና አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ሲሉ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ። አምባሳደር ሬድዋን ይህን ያሉት ትናንት በተካሄደው ሁለተኛው የብሔራዊ ደኅንነት ኮንፈረንስ ላይ ነው። የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፤ ባለፉት ዓመታት የፀጥታ ሁኔታው ተለዋዋጭ፣ኢ-ተገማችና ውስብስብ ክስተቶችን ማስተናገዱን አስታውሰዋል። በአማራና ኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፀረ ሰላም ኃይሎችና አሸባሪ ቡድኖች የተለያዩ ችግሮች ሲፈጥሩ መቆየታቸውንም ነው ያነሱት። የውስጥና የውጭ ጠላቶች ኢትዮጵያን የማያባራ አዙሪት ውስጥ ለማስገባት ሙከራዎች ሲያደርጉ መቆየታቸውንም ጠቅሰዋል። የፀጥታና ደህንነት የተቋማት ስጋቶችን ለመከላከል፣ሕዝቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ ለማስቻል፣ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር፣ውጤታማ ስምሪትና የሕግ ማስከበር እርምጃ በመውሰድ ሀገራዊ ሰላምና ደህንነትን የማረጋገጥ ተልዕኳቸውን በስኬት በመወጣት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሁኔታዎች በፍጥነት እየተለዋወጡ መሆኑን በመጥቀስ፤ በጎረቤት ሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት መባባሱን፣በሶማሊያ እንደ አልሸባብና አይ ኤስ ያሉ አሸባሪዎች ማንሰራራታቸውንና የጥቃት ስልታቸውም እየተለዋወጠ መምጣቱን አንስተዋል። በሌሎችም የክፍለ አህጉሩ ሀገራት የተለያዩ የፀጥታ ስጋቶችና ሁከቶች መጨመራቸውን ነው ያመለከቱት። በዚህ ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነው ዓለም አቀፍ ምህዳር ውስጥ የሀገርን ብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅም ለማረጋገጥ ልቆ መገኘት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ብለዋል። የውስጥ አቅምን በትብብርና በቅንጅት በማሳደግ ለሀገራዊ ተልዕኮ የሚሰማራ ኃይልን ማብዛትና ማጠናከር ተገቢ መሆኑንም ጠቁመዋል። በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት ለቀጣናው አዲስ ስጋት ፈጥሯል ያሉት አምባሳደር ሬድዋን፥በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የባህር በር በሌላቸው ሀገራት ሁኔታውን ውስብስብ አድርጎታል ብለዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር መዳረሻ ለማግኘት በምታደርገው ጥረት ወቅታዊ የጂኦ ፖለቲካዊ አሰላለፎች በፍጥነት ከመቀያየራቸው ባሻገር ቀጣናው በቀይ ባሕር ላይ ተጽዕኖ ለመፍጠር በሚፈልጉ ኃይሎች የፉክክር መናኸሪያ እየሆነ መምጣቱ ተጨማሪ ስጋት ደቅኗል ነው ያሉት። ሁኔታው የኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት ከወደብ በላይ በቀጣናው አስተማማኝ የፀጥታና ደህንነትን የሚያረጋገጥ አንድምታ እንዳለው አመላካች መሆኑንም ጠቅሰዋል። በቀይ ባሕር ተደራሽነት ላይ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማስፈን ሁሉም የቀጣናው ሀገራት በትብብር መስራታቸው አስፈላጊ መሆኑን ለማረጋገጥ በዲፕሎማሲው መስክ የተጀመሩ ተግባራትን አጠናክሮ መቀጠል የግድ ሆኗል ነው ያሉት። ይህ ቁልፍ ብሔራዊ የደኅንነት አጀንዳ እውን እንዲሆን የፀጥታና ደህንነት ተቋማት የትኩረት መስካቸውን ከወቅታዊና ዘላቂ ፍላጎቶች አኳያ በመቃኘት የበኩላቸውን ሚና የመወጣት ወሳኝ ድርሻ አላቸው ብለዋል። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ፀጥታ እንዲሰፍን፣ብሔራዊ ጥቅሞቿ እውን እንዲሆኑ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷ እንዲያድግ እየሠራ ነው ብለዋል። በሰው ኃይል፣በአሠራር፣ በአደረጃጀትና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተቋማዊ ቁመናውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በለውጥ ሂደት ላይ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት አጀንዳዎችን ለማሳካት ከሁሉም የፌዴራልና የክልል ባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርገውን ቅንጅታዊ አሠራር የጋራ ስምሪትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰዋል። ተመሳሳይ ጥቅምና የጋራ ዓላማ ካላቸው የሌሎች ሀገራት አጋር አካላት ጋር ትብብሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም እንዲሁ። ቀጣናው ባለብዙ ፍላጎቶች ያሉበት ስትራቴጂክ ስምሪት የሚካሄድበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የፈጠሩትን አጋጣሚ ለራሳቸው ጥቅም ለማዋል እየሞከሩ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያንም ለማዳከም የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ አጠናክረው መቀጠላቸውን መገንዘብ እንደሚገባ ጠቅሰዋል። በመሆኑም የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን እጅ ለእጅ ተያይዞ ለመሻገር በሲቪል፣ በፀጥታና በዜጎች መካከል ትብብርን ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባና የሸገር ከተማ የነዋሪዎችና የጸጥታ መዋቅር ቅንጅት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ረገድ ተጨባጭ ውጤት እየስገኘ ነው
Apr 3, 2026 545
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባና የሸገር ከተማ የነዋሪዎችና የጸጥታ መዋቅር ቅንጅት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ረገድ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኘ መሆኑን የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ገለጹ። "ሕብረ-ብሔራዊነታችን ለአብሮነታችንና ለሰላማችን" በሚል መሪ ሐሳብ የአዲስ አበባና የሸገር ከተማ ነዋሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና የልምድ ልውውጥ መድረክ በአድዋ ድል መታሰቢያ ተካሄዷል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ደኔሮ፣ የሸገር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጉዮ ገልገሎን ጨምሮ የሁለቱ ከተሞች ከፍተኛ የሰላምና ጸጥታ ዘርፍ አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ነዋሪዎችና የጸጥታ መዋቅሩ በቅንጅት በመንቀሳቀሳቸው ለሰላምና ጸጥታ መረጋገጥ ጉልህ ሚና ተጫውተዋል፡፡ በተለይም ወሰን ተሻጋሪ ወንጀሎችንና ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን በመግታት ረገድ የተከናወኑ ውጤታማ የቅንጅት ተግባራት ለተመዘገበው ስኬት ተጠቃሽ መሆናቸውን አመልክተዋል። በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች መካከል ያለው የጸጥታ መዋቅርና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ከመቼውም ጊዜ በላይ መጠናከሩን ጠቁመው በቀጣይም ይበልጥ ስኬታማ ለመሆን ይህ አንድነትና ሕብረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ መስኮች ሕዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ሕዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰው የተመዘገቡ ስኬቶችን በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ለሰላም ዘብ ሊቆሙ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። በኦሮሚያ ክልል የሸገር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ጉዮ ገልገሎ በበኩላቸው፤ ሰላም የሁሉ ነገር መሰረት ነው፤ ሰርቶ መለወጥ ነግዶ ማትረፍ ወልዶ ማሳደግ የሚቻለው ሰላምን በአስተማማኝ መሰረት ላይ ማስቀመጥ ሲቻል ነው ብለዋል። ለዚህም የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች በጋራ በመስራታቸው ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ረገድ ውጤታማ ስራ መሥራታቸውን ጠቅሰው በቀጣም ይበልጥ መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ደኔሮ በበኩላቸው፤ ሕዝቡ የመረጃ ምንጭ በመሆን ከጸጥታ አካላት እና ሰላም ሰራዊት ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡ ከሸገር ከተማ አስተዳደር ጋር በቅንጅት የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ሀጂ ሸምሱ አባስ በሰጡት አስተያየት መንግሥት በሕዝቦች መካከል አንድነት እንዲጠናከር ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን እየሰራ ያለው ሥራ የሚበረታታ ነው ብለዋል። ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ ፓስተር ጠና በየነ በበኩላቸው፤ የኃይማኖት አባቶች ስለ ሰላም የመስበክ ሚናቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። የልማቱን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሁሉም ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ በአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮና በሸገር ከተማ አስተዳደር በጋራ በተዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ፤ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች፣ ሀደ ስንቄዎች፣ የሰላም ሠራዊት አባላት፣ ጋቸና ሲርና ፣ ሚሊሻዎችና ከሁለቱም ከተሞች የተውጣጡ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት አጀንዳቸውን ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረከቡ
Apr 3, 2026 455
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት ያጠናቀሩትን አጀንዳ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የመጀመሪያ ዙር ከመጋቢት 23 ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲያካሂድ ቆይቷል። በዛሬው እለትም የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት የመጀመሪያው ዙር አጀንዳ ርክክብ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል። በዚህም የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት ያጠናቀሩትን አጀንዳ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች የተጠናቀረውን አጀንዳ ተረክበዋል።
ፖለቲካ
ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረግን ነው
Apr 4, 2026 28
ጅማ ፤መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም በማስቀደም በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረጉ መሆኑን የተለያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ ሃላፊዎች ተናገሩ። የለውጡ መንግስት ባለፉት ዓመታት በዲፕሎማሲ፣ በፖለቲካ፣ ማህበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ ዘርፎች ስኬቶችን በተግባር ያረጋገጠበት ስኬታማ አመት መሆኑን በብዙ ማሳየዎች መግለጽ ይቻላል። የተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ ሰላማዊ ትግል እያደረጉ እና የመንግስት ተቋማትን የመምራት እድል የተሰጣቸው መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም በማስቀደም በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረጉ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች ገልጸዋል። የሸካ ዞን የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ሀይሉ ተስፋዬ፤ ከለውጡ በፊት በፖለቲካው ለመሳተፍ ባደረጉት ጥረት በጠላትነት ተፈርጀውና ተገፍተው መቆየታቸውን አስታውሰው በለውጡ በተፈጠረው ምቹ ምህዳር በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርም በሀገር ብሄራዊ ጥቅም እና የዜጎች ክብር ላይ የጋራ አቋም ያላቸው መሆኑን አንስተው ከማይገባ ተቃርኖ እና የጠላትነት እሳቤ በመውጣት በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። በተፈጠረው ሰፊ የፖለቲካ ምህዳር በሀሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፉክክር እያደረግን ለዘንድሮውም ጠቅላላ ምርጫ ዝግጅት እያደረግን እንገኛለን ብለዋል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) አስተባባሪ አቶ ሰለሞን መኮንን፤ ለውጡ በተለይም የፖለቲካውን ምህዳር በማስፋት እና አሳታፊ በማድረግ የሚታይና ተጨባጭ ውጤት የመጣበት ሆኗል ብለዋል። በፖለቲካ ፉክክሩ በሀገር ብሄራዊ ጥቅም ላይ የጋራ አቋም መኖሩን አንስተው ከገዢው ፓርቲ ጋር ስለ ሀገር እና የዜጎች ጉዳይ ላይ ተቀራርበን እየሰራን እንገኛለን ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ እያደገ እንዲመጣ ኢዜማ የበኩሉን መወጣቱን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የምርጫ ካርድ በመውሰድ ይጠቅመናል ብለን የምናምንበትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል- የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች
Apr 4, 2026 150
ጅግጅጋ፣መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ የምርጫ ካርድ በመውሰድ ይጠቅመናል ብለን የምናምንበትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን ተወስኖ፣ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ስም እንዲሁም የመለያ ምልክት አደራደር ቅደም ተከተል ለመወሰን የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት አካሒዷል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም ፖሊሲና ስትራቴጂያቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የምርጫ ክርክርና የቅስቀሳ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የኢዜአ ሪፖርተር በየምርጫ ጣቢያዎቹ ተዘዋውሮ የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ያሉ ዜጎችን አነጋግሯል። ከየምርጫ ጣቢያዎቹ አስተያየት የሰጡ ነዋሪዎችም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በምርጫው እለት በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ አብዱላሂ ሀሰን እና አቶ ሙክታር ከድር፤ የምርጫ ሂደት የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የሚረጋገጥበት መሆኑን በማንሳት በእለቱ ለሚፈልጉት ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ካርድ ከመያዝ በተጓዳኝ ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት ሁላችንም የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናልም ብለዋል። ሌላኛው የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኘናቸው አቶ መታን አብዲራህማን፤ የዘንድሮው የምርጫ ሂደት እስካሁን የተቀላጠፈ እና ዘመናዊ አገልገሎት የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በምርጫው እለት ድምፃቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የመራጮች የምዝገባ ሂደት እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከናወን መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ያወጣው የጊዜ ሰሌዳ ያመለክታል።
በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ተዘጋጅተናል- የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች
Apr 3, 2026 1193
ጋምቤላ ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ዘንድሮ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ሲወስዱ ያገኘናቸው የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በንቃት ለመሳተፍ ተዘጋጅተዋል፡፡ አስተያየታቸውን ከሰጡን የከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ኮንግ ቾል እንዳሉት ዘንድሮ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን ካርድ በወቅቱ ወስደዋል፡፡ ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ መያዛቸው የምርጫው ጊዜ ሲደርስ የሚፈልጉትንና ለሀገር የሚበጀውን ሀሳብ የያዘውን ፓርቲንም ሆነ እጩ ለመምረጥ መብት እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል፡፡ የወሰዱትን የምርጫ ካርድ በጥንቃቄ በመያዝ ለሀገር ይጠቅማል ብለው ለሚያምኑት እጩ ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ አኙት ኡቹዶ ናቸው፡፡ አቶ አብዱ አቡበክር በበኩላቸው፤ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ጊዜው ከማለፉ በፊት መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ የመራጭነት ካርድ መውሰድ የዜግነት ሃላፊነትን ከመወጣት ባለፈ በሀገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት ለሚደረገው ጥረት አይነተኛ ፋይዳ እንዳለውም አብራርተዋል፡፡ ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ሀገራዊ ለውጡ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት በተደመረ አቅም ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ አስችሏል-የፀጥታና ደኅንነት ከፍተኛ አመራሮች
Apr 3, 2026 907
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተቋማት የተደረገው ሪፎርም ጠንካራ የፀጥታና ደህንነት ተቋማት በመፍጠር በተደመረ አቅም ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ ማስቻሉን የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ። ሀገራዊ፣ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የፀጥታና ደኅንነት ምህዳሩን የገመገመው ብሔራዊ የደኅንነት ኮንፈረንስ ተካሂዷል። በኮንፈረንሱ የተሳተፉ የፀጥታና ደኅንነት ከፍተኛ አመራሮች በሰጡት ማብራሪያ ተለዋዋጭ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ ያደረገ ሀገራዊ የፀጥታ ምህዳር መገንባቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንዳሉት፥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት መንግሥት ከተገበራቸው የሪፎርም አምዶች አንዱ ጠንካራና ገለልተኛ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት መገንባት ነው። በሪፎርሙም ፌዴራል ፖሊስን ጨምሮ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት በሰው ኃይል፣በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በአደረጃጀት የላቁ እንዲሆኑ መደረጋቸውን ተናግረዋል። የለውጥ እርምጃዎች በሀገሪቱ ያለውን ፀጥታና ሰላም ለማፅናትና በቀጣይም ተልዕኮዎችን ለመሸከም የሚያስችል ተቋማዊ አቅም መፍጠር ያስቻሉ መሆኑንም ተናግረዋል። ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገራት ጭምር አለኝታ የሆኑ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት መገንባታቸውንም አብራርተዋል። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላ በበኩላቸው፥ ሀገራዊ የፀጥታ፣የመረጃና የደኅንነት ምህዳሩ በተቀናጀ አግባብ በስኬታማነት እየተመራ መሆኑን ተናግረዋል። በሪፎርሙ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ከተከፋፈለ አስተሳሰብ ወጥተው በተደመረ አቅም ሀገራዊ ደህንነትን ማረጋገጥ የሚያስችል የላቀ ብቃት ፈጥረዋል ነው ያሉት። የዘርፉ ሪፎርም ቀጣይነት ባለው መልኩ እየተካሄደ መሆኑንና በተለይ ባለፉት አምስት ዓመታት ከፍታ ላይ መድረሱን ተናግረዋል። የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት የተለያዩ ፈተናዎችን በውጤታማነት በማለፍ እየተጠናከሩ መምጣታቸውንም ገልፀዋል። ተቋማቱ ሀገራዊ፣ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ተልዕኳቸውን በአስተማማኝ ሁኔታ በመወጣት ላይ እንደሚገኙ አንስተዋል። የኦሮሚያ አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ፥ ሀገራዊ ለውጡ በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት መካከል ቅንጅታዊ አሠራርን ያጠናከረ ምህዳር መፍጠሩን ተናግረዋል። በክልል ደረጃም የነበሩ የፀጥታ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱና የሕግ የበላይነት በማስፈን ረገድ ከፍተኛ አቅምና ውጤት ያመጣ ነው ብለዋል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግሥቴ (ዶ/ር) ተቋማዊ ሪፎርሙ ሀገሪቱ ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚገጥማትን የፀጥታና ደኅንነት ጥቃት በብቃት ለመመከት የሚያስችል አቅም መፍጠሩን ተናግረዋል። የፀጥታና ደኅንነት ሪፎርሙ ተናባቢና ተደጋጋፊ ተቋማትን መፍጠር ያስቻለ መሆኑንም ነው የገለፁት። የፀጥታና ደኅንነት አመራሮቹ አክለውም ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የፀጥታና የደኅንነት ግብረ ኃይል እቅድ በማዘጋጀት እየሠሩ መሆኑን ገልፀዋል። በሀገሪቱ አስተማማኝ ሰላምና ደኅንነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት የተከናወኑ ተግባራት ምርጫውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የሚያስችል አቅምና ዕድል መፍጠራቸውን አስረድተዋል። ከስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተሞክሮ በመነሳት፥ባለፉት ስምንት ወራት የፀጥታ መዋቅሩ የጋራ እቅድ አዘጋጅቶ ከፌዴራል እስከ ክልል ድረስ በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን ጠቅሰዋል። በዚህም ምርጫውን በተሳካ መንገድ ለማካሄድ ምቹ የፀጥታና ደኅንነት ምኅዳር መፈጠሩን ተናግረዋል። ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ ምንም ዓይነት ስጋት እንዳይፈጠር ተቋማቱ ቅንጅታቸውን አጠናክረው እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።
የትግራይ ክልል የመጀመሪያ ዙር የባለድርሻ አካላት የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ ስኬታማ ነው- ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Apr 3, 2026 729
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል የመጀመሪያው ዙር የባለድርሻ አካላት የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ ስኬታማ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የመጀመሪያ ዙር ከመጋቢት 23 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲያካሂድ ቆይቷል። በመጀመሪያው ዙር የተሳተፉ የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት ያጠናቀሩትን አጀንዳ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፈሰር መስፍን አርዓያ በዚሁ ወቅት፥ የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረኩ በሁሉም አካባቢዎች በተደረጉ ስነ-ዘዴዎች መካሄዱን ገልጸዋል። መድረኩ ስኬታማ መሆኑን ጠቁመው፤ ለመድረኩ ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም በበኩላቸው፤ በመድረኩ ከ700 በላይ ተሳታፊዎች የታደሙ ሲሆን በርካታ ሀሳቦች መንሸራሸራቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)፥ የትግራይ ክልል የባለድርሻ አካላት የመጀመሪያው ዙር የአጀንዳ ማሰባሰብ በስኬት መጠናቀቁን ጠቅሰው፥ በቀጣይም የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ እንደሚኖር ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስከበር በሁሉም መስክ ልቆ መገኘትና ትብብርን ማጠናከር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው
Apr 3, 2026 592
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያንና የቀጣናውን ደኅንነትና ጥቅም ለማስከበር በሁሉም መስክ ልቆ መገኘትና ትብብርን ማጠናከር ወቅታዊና አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ሲሉ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ። አምባሳደር ሬድዋን ይህን ያሉት ትናንት በተካሄደው ሁለተኛው የብሔራዊ ደኅንነት ኮንፈረንስ ላይ ነው። የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፤ ባለፉት ዓመታት የፀጥታ ሁኔታው ተለዋዋጭ፣ኢ-ተገማችና ውስብስብ ክስተቶችን ማስተናገዱን አስታውሰዋል። በአማራና ኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፀረ ሰላም ኃይሎችና አሸባሪ ቡድኖች የተለያዩ ችግሮች ሲፈጥሩ መቆየታቸውንም ነው ያነሱት። የውስጥና የውጭ ጠላቶች ኢትዮጵያን የማያባራ አዙሪት ውስጥ ለማስገባት ሙከራዎች ሲያደርጉ መቆየታቸውንም ጠቅሰዋል። የፀጥታና ደህንነት የተቋማት ስጋቶችን ለመከላከል፣ሕዝቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ ለማስቻል፣ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር፣ውጤታማ ስምሪትና የሕግ ማስከበር እርምጃ በመውሰድ ሀገራዊ ሰላምና ደህንነትን የማረጋገጥ ተልዕኳቸውን በስኬት በመወጣት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሁኔታዎች በፍጥነት እየተለዋወጡ መሆኑን በመጥቀስ፤ በጎረቤት ሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት መባባሱን፣በሶማሊያ እንደ አልሸባብና አይ ኤስ ያሉ አሸባሪዎች ማንሰራራታቸውንና የጥቃት ስልታቸውም እየተለዋወጠ መምጣቱን አንስተዋል። በሌሎችም የክፍለ አህጉሩ ሀገራት የተለያዩ የፀጥታ ስጋቶችና ሁከቶች መጨመራቸውን ነው ያመለከቱት። በዚህ ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች በሆነው ዓለም አቀፍ ምህዳር ውስጥ የሀገርን ብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅም ለማረጋገጥ ልቆ መገኘት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ብለዋል። የውስጥ አቅምን በትብብርና በቅንጅት በማሳደግ ለሀገራዊ ተልዕኮ የሚሰማራ ኃይልን ማብዛትና ማጠናከር ተገቢ መሆኑንም ጠቁመዋል። በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት ለቀጣናው አዲስ ስጋት ፈጥሯል ያሉት አምባሳደር ሬድዋን፥በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የባህር በር በሌላቸው ሀገራት ሁኔታውን ውስብስብ አድርጎታል ብለዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር መዳረሻ ለማግኘት በምታደርገው ጥረት ወቅታዊ የጂኦ ፖለቲካዊ አሰላለፎች በፍጥነት ከመቀያየራቸው ባሻገር ቀጣናው በቀይ ባሕር ላይ ተጽዕኖ ለመፍጠር በሚፈልጉ ኃይሎች የፉክክር መናኸሪያ እየሆነ መምጣቱ ተጨማሪ ስጋት ደቅኗል ነው ያሉት። ሁኔታው የኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት ከወደብ በላይ በቀጣናው አስተማማኝ የፀጥታና ደህንነትን የሚያረጋገጥ አንድምታ እንዳለው አመላካች መሆኑንም ጠቅሰዋል። በቀይ ባሕር ተደራሽነት ላይ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማስፈን ሁሉም የቀጣናው ሀገራት በትብብር መስራታቸው አስፈላጊ መሆኑን ለማረጋገጥ በዲፕሎማሲው መስክ የተጀመሩ ተግባራትን አጠናክሮ መቀጠል የግድ ሆኗል ነው ያሉት። ይህ ቁልፍ ብሔራዊ የደኅንነት አጀንዳ እውን እንዲሆን የፀጥታና ደህንነት ተቋማት የትኩረት መስካቸውን ከወቅታዊና ዘላቂ ፍላጎቶች አኳያ በመቃኘት የበኩላቸውን ሚና የመወጣት ወሳኝ ድርሻ አላቸው ብለዋል። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ፀጥታ እንዲሰፍን፣ብሔራዊ ጥቅሞቿ እውን እንዲሆኑ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷ እንዲያድግ እየሠራ ነው ብለዋል። በሰው ኃይል፣በአሠራር፣ በአደረጃጀትና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተቋማዊ ቁመናውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በለውጥ ሂደት ላይ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት አጀንዳዎችን ለማሳካት ከሁሉም የፌዴራልና የክልል ባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርገውን ቅንጅታዊ አሠራር የጋራ ስምሪትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰዋል። ተመሳሳይ ጥቅምና የጋራ ዓላማ ካላቸው የሌሎች ሀገራት አጋር አካላት ጋር ትብብሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም እንዲሁ። ቀጣናው ባለብዙ ፍላጎቶች ያሉበት ስትራቴጂክ ስምሪት የሚካሄድበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የፈጠሩትን አጋጣሚ ለራሳቸው ጥቅም ለማዋል እየሞከሩ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያንም ለማዳከም የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ አጠናክረው መቀጠላቸውን መገንዘብ እንደሚገባ ጠቅሰዋል። በመሆኑም የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን እጅ ለእጅ ተያይዞ ለመሻገር በሲቪል፣ በፀጥታና በዜጎች መካከል ትብብርን ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባና የሸገር ከተማ የነዋሪዎችና የጸጥታ መዋቅር ቅንጅት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ረገድ ተጨባጭ ውጤት እየስገኘ ነው
Apr 3, 2026 545
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባና የሸገር ከተማ የነዋሪዎችና የጸጥታ መዋቅር ቅንጅት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ረገድ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኘ መሆኑን የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ገለጹ። "ሕብረ-ብሔራዊነታችን ለአብሮነታችንና ለሰላማችን" በሚል መሪ ሐሳብ የአዲስ አበባና የሸገር ከተማ ነዋሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና የልምድ ልውውጥ መድረክ በአድዋ ድል መታሰቢያ ተካሄዷል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ደኔሮ፣ የሸገር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጉዮ ገልገሎን ጨምሮ የሁለቱ ከተሞች ከፍተኛ የሰላምና ጸጥታ ዘርፍ አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ነዋሪዎችና የጸጥታ መዋቅሩ በቅንጅት በመንቀሳቀሳቸው ለሰላምና ጸጥታ መረጋገጥ ጉልህ ሚና ተጫውተዋል፡፡ በተለይም ወሰን ተሻጋሪ ወንጀሎችንና ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን በመግታት ረገድ የተከናወኑ ውጤታማ የቅንጅት ተግባራት ለተመዘገበው ስኬት ተጠቃሽ መሆናቸውን አመልክተዋል። በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች መካከል ያለው የጸጥታ መዋቅርና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ከመቼውም ጊዜ በላይ መጠናከሩን ጠቁመው በቀጣይም ይበልጥ ስኬታማ ለመሆን ይህ አንድነትና ሕብረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ መስኮች ሕዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ሕዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰው የተመዘገቡ ስኬቶችን በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ለሰላም ዘብ ሊቆሙ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። በኦሮሚያ ክልል የሸገር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ጉዮ ገልገሎ በበኩላቸው፤ ሰላም የሁሉ ነገር መሰረት ነው፤ ሰርቶ መለወጥ ነግዶ ማትረፍ ወልዶ ማሳደግ የሚቻለው ሰላምን በአስተማማኝ መሰረት ላይ ማስቀመጥ ሲቻል ነው ብለዋል። ለዚህም የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች በጋራ በመስራታቸው ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ረገድ ውጤታማ ስራ መሥራታቸውን ጠቅሰው በቀጣም ይበልጥ መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ደኔሮ በበኩላቸው፤ ሕዝቡ የመረጃ ምንጭ በመሆን ከጸጥታ አካላት እና ሰላም ሰራዊት ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡ ከሸገር ከተማ አስተዳደር ጋር በቅንጅት የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ሀጂ ሸምሱ አባስ በሰጡት አስተያየት መንግሥት በሕዝቦች መካከል አንድነት እንዲጠናከር ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን እየሰራ ያለው ሥራ የሚበረታታ ነው ብለዋል። ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ ፓስተር ጠና በየነ በበኩላቸው፤ የኃይማኖት አባቶች ስለ ሰላም የመስበክ ሚናቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። የልማቱን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሁሉም ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ በአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮና በሸገር ከተማ አስተዳደር በጋራ በተዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ፤ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች፣ ሀደ ስንቄዎች፣ የሰላም ሠራዊት አባላት፣ ጋቸና ሲርና ፣ ሚሊሻዎችና ከሁለቱም ከተሞች የተውጣጡ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት አጀንዳቸውን ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረከቡ
Apr 3, 2026 455
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት ያጠናቀሩትን አጀንዳ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የመጀመሪያ ዙር ከመጋቢት 23 ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲያካሂድ ቆይቷል። በዛሬው እለትም የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት የመጀመሪያው ዙር አጀንዳ ርክክብ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል። በዚህም የትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት ያጠናቀሩትን አጀንዳ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች የተጠናቀረውን አጀንዳ ተረክበዋል።
ማህበራዊ
የጤና ነገር ...
Apr 3, 2026 385
በዮሐንስ ደርበው የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። የኒውትሬሽን ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ የሰው ልጅ የሰውነት ክፍል 60 በመቶው ውኃ እንደመሆኑ ለተስተካከለ ጤና ሚዛን መጠበቅ በቂ ውኃ መጠጣት ይገባል። ውኃን በትክክለኛው መጠንና ጊዜ መውሰድ ከተቻለ የኩላሊት ህመም ተጋላጭነትን 50 በመቶ መቀነስ እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ነገር ግን ሰውነት የሚፈልገውን የውኃ መጠን በአግባቡ ካላገኘ ለዕለታዊ እና በጊዜ ሂደት ሥር ለሚሰድዱ ህመሞች የመጋለጥ ዕድል እንደሚጨምርም ያነሳሉ። ለመሆኑ ሰውነት የሚፈልገውና በቂ የውኃ መጠን የሚባለው መጠኑ ስንት ነው? በቂ ውኃ አለመጠጣትስ የሚያስከትለው ችግር ምንድን ነው? በሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎች ላይ የኒውትሬሽን መምህር፣ ተመራማሪ እና ደራሲ ይሁኔ አየለ ምላሽ አላቸው። አንድ ሰው የሚያስፈልገው የውኃ መጠን በዕድሜ፣ ጾታ፣ በሥራ ባሕርይ፣ በመኖርያ አካባቢ፣ እንደ ጤና ሁኔታው እና እንደ ሰውነት ክብደቱ እንደሚወሰንም በምላሻቸው አስገንዝበዋል። ለምሳሌ የስኳር ታማሚዎች፣ የምታጠባ እናት፣ በዕድሜ የገፉ ሰዎች፣ ብዙ አድካሚና ላብ የሚያወጡ፣ በሞቃታማ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች በቀን 3 ሊትር ውኃ መጠጣት አለባቸው ይላሉ። በአማካይ ግን በቀን አንድ ሰው ከ2 እስከ 3 ሊትር ውኃ መጠጣት እንደሚጠበቅበት ይገልጻሉ። ጤናማ ሕይወት የሚመሠረተው ከውኃ ነው፤ ለምሳሌ ውኃማውን 60 በመቶ የሰውነት ክፍል ሚዛን ለማስጠበቅ የግድ አስፈላጊውን መጠን ውኃ መጠጣት እንደሚገባ ይመክራሉ። በሰውነት ውስጥ የሚካሄደው ሕይወታዊ ሂደት (ባዮሎጂካል ፕሮሰስ) ውኃን መሠረት ያደረገ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለምሳሌ ለተስተካከለ የሥርዓተ-ምግብ ሂደት፣ ቆሻሻን ከሰውነት አጣርቶ ለማስወጣት፣ የአጥንት መገጣጠሚያ ሥራን ለማስተካከል እና ለሌሎችም በርካታ የሰውነት ክፍሎች የተሳለጠ ተግባር ውኃ ቁልፍ መሆኑን አንስተዋል። ይህን ተከትሎም ውኃ ካሎሪ አልባው መድኃኒት (ተፈጥሯዊው መድኃኒት) እስከመባል መድረሱን ነው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ያስረዱት። ሰውነት የሚያስፈልገውን ያህል ውኃ አለመጠጣት ግን ድካም ያስከትላል፤ ለማየት፣ ለመንቀሳቀስ፣ ለመሥራት፣ ለማሰብ፣ ለመረጋጋት . . . አያስችልምና ሲሉ ያብራራሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንድ ሰው ውኃ የመጠማት መጠኑ ከአራት በመቶ በላይ ከሆነ ለሞት ሊጋለጥ እንደሚችልም ጠቅሰዋል። ውኃ አለመጠጣት፤ የጨጓራ ህመምን በማባባስ ማስገሳት፣ የቆዳ ድርቀትና ግርጣት፣ የኩላሊት ህመም ሌሎች የሰውነት ክፍሎችም ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሠሩ ያደርጋል ነው ያሉት። ከምግብ በፊት 30 ደቂቃ ቀድሞ ውኃ መጠጣት ውፍረትን ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በቂ ውኃ ከመጠጣት በተጨማሪ ፍራፍሬዎችንና አትክልቶችን ማዘውተር እንደሚመከርም ገልጸዋል። የፈላ ውኃ እና የዝናብ ውኃን በብዛት መጠጣት በሰውነት ውስጥ ያሉ ንጥረ ነገሮችን በማስወገድና በኩላሊት ላይም ጫና እንደሚፈጥር አመላክተዋል። ለተስተካከለ ጤናማ ሕይወት የግድ ውኃ መጠጣትን ልማድ ማድረግ እንደሚገባም ይመክራሉ። #ውኃ_መጠጣት #ጤና #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency
በአማራ ክልል 1 ሺህ 224 የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንዲፈቱ ተወሰነ
Apr 3, 2026 107
ባህር ዳር፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል 1 ሺህ 224 የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንዲፈቱ መወሰኑን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አያሌው አባተ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ በይቅርታው ተጠቃሚ የሆኑት ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው የባህሪ ለውጥ ያመጡና የይቅርታ መመሪያውን ያሟሉ ናቸው ብለዋል። በተጨማሪም እርቅና ካሳ የፈፀሙ፣ በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ታንፀው መልካም ስነ- ምግባር ያሳዩ የሚገኙበት መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት 1 ሺህ 224 የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንዲፈቱ መወሰኑን ተናግረዋል። በመሆኑም ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ የወንጀልን አስከፊነት ከማስተማር ባለፈ የበደሉትን ለመካስና የልማት አርበኛ እና የሰላም አምባሳደር ሆነው ለማገልገል መዘጋጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የሚዲያ ተቋማት የምርጫ ሂደት ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የላቀ ድርሻ አላቸው
Apr 3, 2026 126
ሆሳዕና ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የሚዲያ ተቋማት የምርጫ ሂደት ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የላቀ ድርሻ እንዳላቸው ተመለከተ። "የሚዲያ ተቋማት ሚና ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ" በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በማህበራዊ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ በምርጫ ሂደት የሚዲያ ተቋማት ሚና እና ሃላፊነት እንዲሁም መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች በስፋት ተነስቶ ውይይት ተደርጎበታል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ዲን ታደለ አባተ፤ የሚዲያ ተቋማት ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ በምርጫ ወቅት እና በድህረ ምርጫ ሂደት ግልጽና ፍትሃዊ መሆኑን የማሳየት ሃላፊነት ያለባቸው መሆኑን አንስተዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን አማራጭ ፖሊሲና ፕሮግራም ለህዝብ ተደራሽ በማድረግ የጠራ ግንዛቤ እንዲይዙ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል። በምርጫ ሂደት ለግጭት ምክንያት የሚሆኑ፣ የጥላቻ ንግግሮችንና የተሳሳቱ መረጃዎችን በማጋለጥ እውነታን በማረጋገጥ እንዲሁም እውነተኛና ሚዛናዊ የመረጃ ምንጭ በመሆን ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። በመድረኩ ላይ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የልማት ጥናትና የጋዜጠኝነት መምህርና ተመራማሪ መልሰው ደጀኔ (ዶ/ር)፤ የሚዲያ ተቋማት የምርጫ ሂደት ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል። ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ ያሉትን ሂደቶች በተጨባጭ መረጃ በማስደገፍና እውነታዎችን በማረጋገጥ ተደራሽ የማድረግ ሃላፊነት አለባቸው ብለዋል። በአጠቃላይ በምርጫ ሂደት የዴሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የሚዲያ ተቋማት እውነተኛና ሚዛናዊ የመረጃ ምንጭ በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል። በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሰላምና ደህንነት ትምህርት መምህርና ተመራማሪ ተመስገን ቶማስ (ዶ/ር)፤ የሚዲያ ተቋማት የሀሳብ ብዝሀነትን በማስተናገድ የዴሞክራሲ ምህዳርን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው አመልክተዋል። የጋራ ትርክትን በሚያጠናክሩና የሀገርን ሁለንተናዊ ለውጥ የሚያሳልጡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር መስራት ይገባል ሲሉም አንስተዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አብድልባር ኡስማን፤ በክልሉ መገናኛ ብዙሃን ለዘንድሮው የምርጫ ሂደት ስኬታማነት የላቀ ሚናቸውን በመወጣት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። በምክክር መድረኩ ላይ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና ምሁራን ተሳትፈዋል።
በክልሉ ጠንካራ የሲቪል ሰርቪስ ተቋም በመገንባት ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ተደርጓል
Apr 3, 2026 86
ደብረ ብርሃን ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ጠንካራ የሲቪል ሰርቪስ ተቋም በመገንባት ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት መደረጉን የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የአስተዳደር ፍርድ ቤት የዳኞች ጉባኤ ምስረታን ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ አካሄዷል፡፡ የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ባንችአምላክ ገብረማርያም እንደገለጹት፤ ጠንካራ ሲቪል ሰርቪስ ተቋምን በመገንባት ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ተደርጓል። በአሁኑ ወቅትም የመንግስት አገልግሎት አስተዳደር ሪፎርም በመዘርጋት ነፃና ገለልተኛ የሲቪል ሰርቪስ ተቋም ለመገንባት እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም የአስተዳደር ዳኝነት ስርዓቱን ዲጂታላይዝ ማድረግና የአስተዳደር ፍርድ ቤት የዳኞች ጉባኤን ማቋቋሙን አንስተዋል። የሲቪል ሰርቪስ ግንባታው አካታችነትን ያረጋገጠና የሰራተኛውን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ቀደም ሲል የሰራተኞች የአስተዳደር ፍርድ ቤት ዳኞች ውሳኔ የሚጸድቀው በሌላ አካል እንደነበር ጠቁመው በአዲሱ አሰራር ገለልተኛ የሆነ አግባብ ተቋቁሞ እንዲሰራ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፤ የሲቪል ሰርቪስ አሰራሩን በማዘመን ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ እየተሰራ ነው ብለዋል። የአስተዳደር ፍርድ ቤት የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ መመስረቱም በሰራተኞች የሚነሱ የመብትና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄዎችን ህግን መሰረት ባደረገ አግባብ ለመመለስ የሚረዳ መሆኑን አመልክተዋል። በክልሉ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ተጠሪ ዳኛ አቶ ስለሺ አብርሃም እንዳሉት፤ በክልሉ የሲቪል ሰርቪስ የዳኝነት ስርዓትን ነፃ ገለልተኛና ተጠያቂ ማድረግ ጠንካራ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት ይረዳል ብለዋል። አሁን የተመሰረተው የዳኞች ጉባኤ በሰራተኞች የሚነሱ የጥቅማ ጥቅም፣ የመብትና ግዴታ ውል ጉዳዮችን ራሱን ችሎ በማከራከር ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርም አስረድተዋል። መድረኩ ዘጠኝ አባላት ያሉት የአስተዳደር ፍርድ ቤት የዳኞች ጉባኤ አባላትን በመምረጥ ተጠናቅቋል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደንበኞችን እርካታ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አሰራሮችን እየተገበረ ነው
Apr 4, 2026 46
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ግልጽነትንና ተጠያቂነትን በማስፈን የደንበኞችን እርካታ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አሰራሮችን እየተገበረ እንደሚገኝ ገለጸ። መንግሥት የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እንዲሰጡ የሪፎርም ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም እንደ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያሉ በአጭር ጊዜ የህዝብን የእርካታ መጠን ማረጋገጥ የቻሉ ተቋማትን መገንባት ተችሏል። ይህን መሰረት በማድረግ ሌሎች የመንግሥት ተቋማትም አሰራራቸውን በማዘመንና ከህዝብ ጋር በመቀራረብ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የሚያስችል ስልት እየተከተሉ ይገኛል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ዳይሬክተር ህብረወርቅ ይመኑ፣ ተቋሙ የደንበኞችን እርካታ ለማሳደግ የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ደንበኞች በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚገጥሟቸውን ብልሹ አሰራሮችን በምስጢር መጠቆም የሚችሉበትን ቀላል፣ ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀ መተግበሪያ ስራ ላይ ማዋሉን አስታውቀዋል። በዚህም ደንበኞች "eeuethics.et" በተሰኘው ድረ-ገጽ በመግባት ወይም መተግበሪያውን ስልካቸው ላይ በመጫን ቅሬታቸውንና ጥቆማቸውን በቀላሉ ማቅረብ እንደሚችሉ ገልጸዋል። መተግበሪያው የደንበኞችን የጥቆማ ተሳትፎ ማሳደግ የቻለ ሲሆን፣ ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ 374 ጥቆማዎች መቅረባቸውን አብራርተዋል። ከጥቆማዎች መካከል በማጣራትም በተገኙ ግኝቶች መሠረት በ98 ሰራተኞች ላይ ህጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። ተቋሙ ለጠቋሚዎች ተገቢውን ጥበቃ በማድረግ ብልሹ አሰራሮችን በድፍረት እንዲያጋልጡ የሚያስችል የእውቅና አሰጣጥና የጥበቃ መመሪያ አዘጋጅቶ ወደ ሥራ ማስገባቱንም ገልጸዋል። የአሰራር ስርዓትን በቴክኖሎጂ ከማዘመን ባለፈም የሰራተኞችን የስነ-ምግባር ሁኔታ ለመለየት የሚያስችል ልዩ ማዕቀፍ መዘጋጀቱን አስረድተዋል። ደንበኞች ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉና ለማንኛውም አገልግሎት ክፍያ ሲፈጽሙ ህጋዊ ደረሰኝ የመቀበል ግዴታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
ለግብርና ትራንስፎርሜሽንና ሜካናይዜሽን የተሰጠው ትኩረት ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ መሰረት እየጣለ ነው
Apr 4, 2026 90
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለግብርና ትራንስፎርሜሽንና ሜካናይዜሽን የሰጠችው ትኩረት ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ መሰረት እየጣለ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ። የ2018/19 የሰብል ልማት ንቅናቄ "በምርትና ምርታማነት የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው። የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ መፃኢ ጊዜ የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ አኳያ ብሩህ ነው። በመደመር መንግሥት የተጀመረው የግብርና ትራንስፎርሜሽን እንቅስቃሴ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ በተጨባጭ ውጤት መታየት መጀመሩን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ግብርና ዘመናዊ በማድረግ ወደ ሜካናይዜሽን እየተሸጋገረ መምጣቱን ገልጸው፤ በኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው ተግባር ተጨባጭ ለውጥ መታየቱን ተናግረዋል። የ2018/19 የመኸርና የበጋ ሰብል ልማት ወቅት በዓለም አቀፍ ቀውስ ፈተና ውስጥ ሆና የሚካሄድ መሆኑን ገልጸው፤ ነገር ግን የአፈር ማዳበሪያ ቀድሞ በማስገባት ስጋቱን መሻገር መቻሉን ገልጸዋል። በተለይም የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት የሎጂስቲክ ስርዓቱን ላይ የሚያደርሰውን ጫና ለመቋቋም ሌት ተቀን በትጋት መሥራት ይገባናል ብለዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየርንበትን ልምድ ዛሬም ማስቀጠል ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ጌቱ ገመቹ በበኩላቸው፤ በክልሉ ከ33 በላይ ኢኒሼቲቭ ተግባራዊ ተደርጓል ብለዋል። ክልሎች ያላቸውን የተፈጥሮ ጸጋ በአግባቡ በመተግበር በትጋት መስራት ከተቻለ ለውጥ እንደሚመጣ ኢንሼቲቮች በተግባር ማሳየታቸውን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች ያሉ ልምዶችን በመውሰድ ዝርያዎችን በማላመድ ዓይነት ብዙ ምርቶችን ማምረት መጀመሩን ገልጸው፤ ከአማራ ክልል ልምድ በመቅሰም ሩዝ ማምረት መቻሉን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ የአፈር ማዳበሪያ ግዥ በመፈጸም አስገብታለች
Apr 4, 2026 123
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኢ- ተገማችና ተለዋዋጭ ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ ቀደም ብላ የአፈር ማዳበሪያ ግዥ በመፈጸም ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባቷን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ። በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ጦርነትና ዓለም አቀፍ ቀውስ የምርቶች ግዥና ዝውውር ላይ ችግር መፍጠሩ ይታወቃል። የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ የአፈር ማዳበሪያ ከሚጓጓዝባቸው መስመሮች መካከል የመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና አንዱ መሆኑን ጠቅሰው ጦርነቱ በመርከቦች እንቅስቃሴ ላይ ፈተና መደቀኑን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ መንግሥት ዓለም አቀፍ ኢ-ተገማችና ተለዋዋጭ ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ ማዳበሪያን በተመለከተ ቀደም ብሎ ዝግጅት በማድረግ ወደ ሥራ መግባቱን ተናግረዋል። በዚህም ለዘንድሮ የምርት ዘመን የሚውል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ በመፈጸምና በማጓጓዝ ወደ ህብረት ስራ ዩኒየኖችና አርሶ አደሮች ተደራሽ ማድረጉን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት የምርት ዘመን ለአርሶ አደሩ የተሰራጨው የአፈር ማዳበሪያ 16 ነጥብ 9 ሚሊየን ኩንታል እንደነበር ገልጸው፤ ጅቡቲ የደረሰውን ጨምሮ ዘንድሮ 20 ሚሊየን ኩንታል ማዳበሪያ ገብቷል ብለዋል። የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥና የግብዓት አጠቃቀምን ለማሻሻል 30 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት መታቀዱን በመጥቀስ፤ ቀሪውን ለማሳካት ከወዳጅ ሀገራት ጋር ጠንካራ ትብብርና ስምምነት መፈጠሩን ገልጸዋል። የምግብ ሉዓላዊነት የህልውና ጉዳይ መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሩ፤ የግብርና ልማት ሰንሰለት ውስጥ ከምርት እስከ እሴት መጨመርና ገበያ ድረስ ያለውን ሂደት መቆጣጠር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ከዚህ አንፃር ኢትዮጵያ የጀመረችው የአፈር ማዳበሪያ ማምረቻ ግንባታ በተለዋዋጭና ኢ-ተገማች የዓለም ሁኔታ ሊገጥሙ የሚችሉ ፈተናዎችን በድል መወጣት የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ አርሶ አደሮች በተፈጥሮ በሚዘጋጁ የኮምፖስት ማዳበሪያ ምርቶች ላይ በስፋት በመሰማራት ጫናውን መቀነስ እንደሚገባቸውም ተናግረዋል።
በክልሉ የበጋ መስኖ ስንዴ ጨምሮ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማትና የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቮች ለምርታማነት እድገት እመርታዊ ለውጥ እያመጡ ነው
Apr 4, 2026 82
ባህርዳር፤ መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የበጋ መስኖ ስንዴ ጨምሮ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማትና የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቮች ለምርታማነት እድገት እመርታዊ ለውጥ እያመጡ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የምርት እድገቱ በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት፣ ለኢንዱስትሪ ግብአትና የወጭ ንግድ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ደረጀ ማንደፍሮ፤ በክልሉ የግብርና ልማት እንቅስቃሴና ምርታማነትን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በክልሉ የግብርና ልማት ከምርት ወቅቶች ባሻገር የበጋ መስኖ ልማትን በስፋት የመጠቀም፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ የሌማት ትሩፋትና ሌሎችም ኢንሼቲቮች ለምርታማነት እድገት እመርታዊ ለውጥ አምጥተዋል ብለዋል። በግብርና ልማቱ በተለይም የኩታገጠምና የመካናይዜሽን እርሻ፣ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አቅርቦት መሟላት ለምርታማነቱ ማደግ ዋናውን ድርሻ መያዙን ጠቅሰዋል። በ2012/2013 የመኸር ወቅት ቀደም ሲል በማካይ ይመረት ከነበረው 121 ነጥብ 7 ሚሊየን ኩንታል አሁን ላይ 188 ሚሊየን ኩንታል ማድረስ መቻሉን ለአብነት ገልጸዋል። በክልሉ የግብርና ልማትና ምርታማነት በአይነትም ይሁን በብዛት ከፍተኛ እድገት እየተመዘገበበት መሆኑን ተናግረዋል። ከሀገራዊ ለውጡ በፊት በክልሉ የመካናይዜሽን እርሻ እንዳልነበር አስታውሰው አሁን ላይ በድምሩ ከ2 ሺህ 888 በላይ ትራክተሮች፣ የሰብል ማጨጃና መውቂያ ኮምባይነሮች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም አነስተኛ የሰብል መውቂያ፣ የሩዝና የበቆሎ መፈልፈያ ማሽኖችን በመጠቀም በግብርና ልማትና ምርታማነት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በአማራ ክልል ከምርት ወቅቶች ባሻገር ማምረት የሚለው አስተሳሰብ ወደ ተግባር እየተቀየረ በመሆኑ፣ ግብርናው ከዝናብ ጥገኝነት ተላቆ ወደ ንግድ ተኮር ግብርና እየተሸጋገረ ይገኛል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በኦሮሚያ ክልል የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚመልሱ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Apr 4, 2026 61
ጅማ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለህዝቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ ገለጹ። በጅማ ዞን ኦሞ ናዳ ወረዳ አሰንዳቦ ከተማ፣ በወረዳ ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። አቶ ነመራ ቡሊ በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሉ በስፋት እየተተገበረ መሆኑንና የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በሂደት ለመመለስ እየተከናወነ ያለ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። አገልግሎቱ ብልሹ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ፣ የህዝቡን ጥያቄዎች አንድ በአንድ እየመለስን ለመሆናችን ማሳያ ነው ያሉት ኃላፊው፣ ወደፊትም አገልግሎቱን በማዘመን ለበርካታ ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የጅማ ዞን አስተዳዳሪ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፣ የዞኑ ነዋሪዎች በተደጋጋሚ የሚያነሷቸውን የልማትና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥያቄዎችን ለመፍታት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በወረዳ ደረጃ እየተስፋፋ መሆኑን ገልጸዋል። የአሰንዳቦ ከተማ አስተዳዳሪ ነዚፍ ሼህ ከማል በማዕከሉ 11 ተቋማት 52 ዓይነት አገልግሎቶች በ8 መስኮቶች እንደሚሰጥ ጠቅሰው ባለሙያዎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ስልጠና ወስደው ወደ ስራ ገብተዋል ብለዋል።
የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የጤና ሥርዓቱን የሚያዘምን አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው
Apr 3, 2026 86
አዲስ አበባ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የጤና ሥርዓቱን የሚያዘምን አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ ገለጹ። በጤና ሚኒስቴር ብሔራዊ የጤና ኢኖቬሽን ማበልፀግያና በሀርቫርድ ጤና ስርዓት ኢኖቬሽን ሃካቶን ትብብር በአዲስ አበባ የተዘጋጀው የ2026 ዓለም አቀፍ የጤና ኢኖቬሽን ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል። ጉባዔው በኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ7ኛ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን "ሰው ሰራሽ አስተውሎት፤ ለላቀ የጤና ሥርዓት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ከዛሬ መጋቢት 25 እስከ 26/2018 ዓ.ም ይቆያል። በዚሁ ጊዜ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ፤ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት የጤና ጥራትና ፍትሐዊ ተደራሽነትን በማጠናከር ከፍተኛ እገዛ እያደረገ ነው ብለዋል። በዲጂታል ዘርፍ የተወሰዱ የሕግና የአሰራር ማሻሻያዎችም የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት በማዘመን ተጨባጭ ውጤቶች ማስገኘታቸውን ገልጸዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መነሻነትም ሀገር በቀል የፈጠራ ክህሎትን በማዳበር የጤና ተቋማትን የማዘመን ሥራ ትኩረት እንደተሰጠው አስረድተዋል። በጤና ሚኒስቴር የዲጂታል ፈጠራ አስቻይ ምኅዳርም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ መዋቅራዊ የአሰራር ለውጥ እየተደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ የጤና ሥርዓቱን ለማዘመን የሚከናወኑ ተግባራት ውጤታማነትን በማሳደግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዲጂታል ምኅዳሩን በማስፋት በዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ የሰው ሃብት የማፍራት ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ለማዘመን በሚደረገው ጥረት የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጥቅም ላይ በማዋል የአገልግሎት ጥራትን በማስጠበቅ የሰውን ህይወት ለመታደግ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በዲጂታል ዘርፍ የተመዘገቡ አስደናቂ የዲጂታል ስኬቶችም ኢትዮጵያ ጉባኤውን ለመጀመሪያ ጊዜ እንድታዘጋጅ ማስቻሉን አስረተድዋል። በጉባኤው ላይ 60 ኢትዮጵያዊያን የጤና ሙያተኞች፣ የሶፍትዌር አልሚዎች፣ ተመራማሪዎችና ተማሪዎች የጤና ሥርዓትን የሚያሻሽሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለውድድር እንደሚያቀርቡም አስታውቀዋል። በቀጣይም የዲጂታል መሰረተ ልማትን በማስፋት የፈጠራና ክህሎት ዝንባሌ ያላቸው ዜጎችን የማብቃት ሥራ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
የሲዳማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ለመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍትሔ እየሰጠ ነው
Apr 2, 2026 109
ሃዋሳ፤ መጋቢት 24/2018(ኢዜአ)፦ የሲዳማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ለመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍትሄ እየሰጠ መሆኑን የይርጋለም ከተማ ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቴክኖሎጂ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትን አገልግሎቶች በአንድ ዲጂታል ሥርዓት በማቀናጀት፣ ደንበኞች እንደ መንጃ ፈቃድ፣ መታወቂያ እና የባንክ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ በቀላሉ እንዲያገኙ ያስችላል። በሲዳማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎትም 17 ተቋማት የገቡ ሲሆን ከ74 በላይ አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑም ተመላክቷል፡፡ የማእከሉ ተገልጋዮች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በቴክኖሎጂ የታገዘው የማእከሉ አገልግሎት ጊዜ፣ ወጪንና እንግልት የቀነሰና ለመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍትሄን የሰጠ ነው፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የይርጋለም ከተማ ነዋሪው አቶ ከበደ አመሎ የመጡበትን ጉዳይ በአስር ደቂቃ ውስጥ መፈጸማቸውን ጠቅሰው ከዚህ ቀደም የነበረው አሰራር የተንዛዛ እንደነበረ አስታውሰዋል፡፡ አገልግሎቱ በዲጂታል የታገዘ መሆኑና የተለያዩ ተቋማት በአንድ ቦታ መገኘታቸው የተገልጋዩን እንግልት ለመቀነስና ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ የማእከሉ አገልግሎት የተገልጋይ እርካታን ከማሳደግ ባለፈ ሀገራዊ ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት አስተያየት ሰጪው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት በመንግስትና ህዝብ መካከልም መተማመን ይፈጥራል ነው ያሉት፡፡ ሌላኛው ተገልጋይ አቶ ዎማ ጋቢሶ በበኩላቸው ውክልና ለመስጠት ወደ ማእከሉ መምጣታቸውን ጠቅሰው በተቋሙ የተፈጠረው አዲስ የስራ እሳቤ የተገልጋዩን ጊዜ፣ ወጪና እንግልት ከመቀነስ ባለፈ በእውቀት እንዲገለገል አስችሏል ብለዋል፡፡ ስለሚያገኙት አገልግሎት የህግ ድጋፍ ጭምር ማግኘታቸውን ጠቅሰው አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ መሆኑና የተለያዩ ተቋማት በአንድ ላይ መኖራቸው አገልግሎቱን ቀልጣፋ እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡ በማእከሉ የሚሰጠው አገልግሎት ፍትሃዊና ከዚህ ቀደም ለሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍትሄን ያመላከተ በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በማእከሉ የሚሰጠው አገልግሎት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን የገለጹት ወይዘሮ መታሰቢያ አለማየሁ በበኩላቸው በአገልግሎት አሰጣጡ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የማእከሉ መከፈት ከዚህ ቀደም ረጅም ጊዜ ወስዶ ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት በ15 ደቂቃ ውስጥ መፈጸም በመቻላቸው ጊዜ፣ ወጪና እንግልትን ቀንሶላቸዋል፡፡ የሲዳማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ እንግዳየሁ ዘውዴ በማእከሉ 17 ተቋማት መኖራቸውንና 74 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እስካሁን ከ35 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች አገልግሎት መሰጠቱን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ የተገልጋዮች እርካታን ለመፈተሽ በተደረገው የዳሰሳ ጥናት ተግባሩ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ከዚህ ቀደም በአገልግሎቱ ዘርፍ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ በመንግስትና ህዝብ መካከል መተማመን እንዲፈጠር እያስቻለ ነው ብለዋል፡፡ በቀጣይም በክልሉ በሚገኙ ሰባት ከተማ አስተዳደሮችና በሃዋሳ ከተማ ተጨማሪ ማዕከል በማቋቋም አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ እቅድ ተነድፎ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሲዳማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት መስከረም 15/2018 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ወደ አገልግሎት መግባቱ ይታወቃል፡፡
የሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ስርነቀል ለውጥ እያመጣ ነው
Apr 1, 2026 532
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2018(ኢዜአ)፦ የሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ስርነቀል ለውጥ እያመጣ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። በመዲናዋ አምስተኛው የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ስራ ማስጀመርያ መርሃ-ግብር ተካሂዷል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መንግስት በመዲናዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነት በማጠናቀቅ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል። የዚሁ አካል የሆነውና የተገልጋዩን እንግልት በመቀነስ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት የሚሰጠው ማዕከል ለአገልግሎት በመብቃቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ሀገራዊ ለውጡ የመንግሥትን አሠራር ስርነቀል በሆነ መልኩ ለቀየረው መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ስኬትና ሌሎቹም ውጤታማ ተግባራት ዋነኛው ምንጭ ነው ብለዋል፡፡ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የሀገራዊ ለውጡ ትሩፋት መሆኑንም ጨምረው ገልፀዋል። ማዕከሉ የተለያዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ስፍራ አቀናጅቶ ጊዜን፣ ወጪን፣ ጉልበትን በመቆጠብ እና እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተለይ ተመጋጋቢ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን በአንድ ማዕከል በማሰባሰብ ዘመናዊ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ብልሹ አሰራሮችን ማስወገድ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አብዛኛው ነዋሪ በንግድ ስራ ላይ የተሰማራ መሆኑን አስታውሰው፤ የሚያጋጥማቸወን እንግልት በማስቀረት ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ውጤታማ እንዲሆኑ ያስችላል ነው ያሉት። አገልግሎቱ በብቁ የሰው ሀይል የተደራጀና ዘመኑን በሚመጥን አስተሳሰብና በላቀ የስራ ተነሳሽነት እንዲሁም በቴክኖሎጂ ለማገልገል መገንባቱን ገልጸዋል። አገልግሎቱ ለመዲናዋ ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲና እና የዲፕሎማሲ ማዕከል እንደመሆኗ በርካታ ስብሰባዎችን ለመታደም የሚመጡ አካላትና ቱሪስቶች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ በሚያስችል ሁኔታ መሰራቱንም ጠቁመዋል።
ስፖርት
የአትሌቲኮ ማድሪድ እና ባርሴሎና የላሊጋ የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ
Apr 4, 2026 88
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፡- በስፔን ላሊጋ የ30ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አትሌቲኮ ማድሪድ እና ባርሴሎና ዛሬ የሚያደርጉት የደርቢ ጨዋታ የእግር ኳስ አፍቃሪያን ትኩረት ስቧል። ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ 70 ሺህ 692 ተመልካች በሚያስተናግደው ዋንዳ ሜትሮፖሊታኖ ስታዲየም ይካሄዳል። አትሌቲኮ ማድሪድ በሊጉ እስከ አሁን ካደረጋቸው 29 ጨዋታዎች በ17ቱ ድል ሲቀናው በስድስቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ ስድስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 49 ግቦችን ሲያስቆጥር 28 ጎሎችን አስተናግዷል። የማድሪዱ ክለብ በ57 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ባርሴሎና በበኩሉ 29 ጨዋታዎችን አከናውኖ በ24ቱ አሸንፎ በአራቱ ሽንፈት አስተናግዶ በቀሪ አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይቷል። 78 ጎሎችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ 28 ግቦች ተቆጥረውበታል። የካታላኑ ክለብ በ73 ነጥብ ሊጉን እየመራ ይገኛል። ሁለቱ ክለቦች በሁሉም ውድድሮች ሲገናኙ የዛሬው ለ254ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ በፊት ባደረጓቸው 253 የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ባርሴሎና 116 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። አትሌቲኮ ማድሪድ 81 ጊዜ ድል ቀንቶታል። 56 ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። በላሊጋው እስከ አሁን 178 ጊዜ ተገናኝተው ባርሴሎና 83 ጊዜ አሸንፏል። አትሌቲኮ ማድሪድ 53 ጊዜ ሲያሸንፍ 42 ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርተዋል። አትሌቲኮ ማድሪድ ማሸነፍ በሻምፒዮንስ ሊግ ለመሳተፍ በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያስገኝለታል። ባርሴሎና ድል ቀናው የሊጉን መሪነት ያጠናክራል። በተያያዘም በ69 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሪያል ማድሪድ ከሜዳው ውጪ ከሪያል ማዮርካ ጋር ከቀኑ 11 ሰዓት ከ15 ላይ ይጫወታል። ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች በላሊጋው የዋንጫ ፉክክር ወሳኝ የሚባሉ ናቸው።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከመቀሌ 70 እንደርታ ጋር ይጫወታል
Apr 4, 2026 62
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደርጋሉ። ምሽት 12 ሰዓት ላይ መቀሌ 70 እንደርታ ከሲዳማ ቡና በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። መቀሌ 70 እንደርታ በሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው 24 ጨዋታዎች በአራቱ አሸንፎ በዘጠኙ ተሸንፎ 11 ጊዜ አቻ ወጥቷል። 15 ግቦችን በጨዋታዎቹ ላይ ሲያሳርፍ 25 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ23 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ተጋጣሚው ሲዳማ ቡና 24 ጨዋታዎችን አከናውኖ 12 ጊዜ ሲያሸንፍ በሶስቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ ዘጠኝ ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 30 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 12 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ሲዳማ ቡና በ45 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። ባለፉት አራት የሊግ ጨዋታዎች ያላሸነፈው መቀሌ 70 እንደርታ ማሸነፍ ከወራጅ ቀጠና ለምወጣት በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያስገኛል። ሲዳማ ቡና ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ እና መሪነቱን ለማጠናከር ይጫወታል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ መድን ከኢትዮጵያ ቡና ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ኢትዮጵያ መድን በውድድር ዓመቱ 24 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስቱን ሲያሸንፍ በስምንቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ 10 ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። 19 ግቦችን በ24ቱ ጨዋታዎች ላይ 15 ግቦችን ሲያስቆጥር 18 ጎሎችን አስተናግዷል። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ28 ነጥብ 14ተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በሊጉ ካከናወናቸው 23 ጨዋታዎች መካከል ዘጠኙን ያሸነፈው ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ በተመሳሳይ ዘጠኝ ጊዜ ተሸንፏል። አምስት ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። 23 ግቦችን ሲያገባ 24 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀራቸው ቡናማዎቹ በ32 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዘዋል። ሁለቱም ቡድኖች ተከታታይ ድላቸውን ለማስመዝገብ ይጫወታሉ። ሀዲያ ሆሳዕና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከቀኑ 7 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ሀዲያ ሆሳዕና በ29 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ25 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ከድል የራቀው ሀዲያ ሆሳዕና ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት ስምንት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ሶስት ነጥብ ከዛሬው ጨዋታ ማግኘት ከወራጅ ቀጠና እንዲወጣ ያደርገዋል። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ወላይታ ድቻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ወላይታ ድቻ በ27 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ30 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በ24ኛ ሳምንት ከመቀሌ 70 እንደርታ ጋር ያለ ግብ አቻ የተለያየው ወላይታ ድቻ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ድል ከቀናው ከወራጅ ቀጠና ይወጣል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካሸነፈ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘግባል።
ተጠባቂው የማንችስተር እና ሊቨርፑል የኤፍኤ ካፕ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ
Apr 4, 2026 78
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ)፡- በኤፍኤ ካፕ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ዛሬ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከቀኑ 8 ሰዓት ከ45 ላይ ማንችስተር ሲቲ ከሊቨርፑል በኢትሃድ ስታዲየም ይጫወታሉ። በጥሎ ማለፉ ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን፣ ሊቨርፑል ዎልቭስን ማሸነፋቸው ይታወቃል። ሁለቱ ክለቦች በኤፍኤ ካፕ ሲገናኙ የአሁኑ ለዘጠነኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው ስምንት ጨዋታዎች ሊቨርፑል በአራቱ ድል ሲቀናው ማንችስተር ሲቲ ሁለት ጊዜ አሸንፏል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኙት እ.አ.አ በ1897 ሲሆን ሊቨርፑል 2 ለ 1 አሸንፏል። በውድድሩ ላይ ለመጨረሻ ጊዜ የተጫወቱት እ.አ.አ በ2022 በግማሽ ፍጻሜው ሲሆን ሊቨርፑል 3 ለ 2 በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፏል። በፍጻሜው ቼልሲን በማሸነፍ ዋንጫውን አንስቷል። ማንችስተር ሲቲ ለመጨረሻ ጊዜ ሊቨርፑልን በኤፍኤ ካፕ ያሸነፈው እ.አ.አ በ2003 ሲሆን በሶስተኛው ዙር 1 ለ 0 አሸንፏል። ሁለቱ ክለቦች በውድድሩ ስኬታማ የሚባሉ ክለቦች ናቸው። ማንችስተር ሲቲ ሰባት ጊዜ ዋንጫውን ሲያነሳ፣ ሊቨርፑል ስምንት ጊዜ ውድድሩን አሸንፏል። ሁለቱ ቡድኖች ለግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ የሚያደርጉት ፍልሚያ የተመልካቾችን ትኩረት ስቧል። በሌላኛው መርሐ ግብር ሳውዝሃምፕተን ከአርሰናል ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሴንት ሜሪ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በጥሎ ማለፉ ሳውዝሃምፕተን ፉልሃምን፣ አርሰናል ማንስፊልድ ታውንን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜ ገብተዋል። ሳውዝሃምፕተን አንድ ጊዜ ውድድሩን አሸንፏል። አርሰናል ዋንጫውን 14 ጊዜ በማንሳት የውድድሩ ስኬታማ ክለብ ነው። ባለሜዳው ሳውዝሃምፕተን በእንግሊዝ ሻምፒዮንሺፕ (ሁለተኛ ዲቪዚዮን) የሚገኝ ሲሆን አርሰናል የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን እየመራ ይገኛል። ሁለቱ ክለቦች ከዚህ ቀደም በውድድሩ ባደረጓቸው 11 ጨዋታዎች አርሰናል ሰባቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። ሳውዝሃምፕተን በሶስቱ ድል ቀንቶታል። በቀሪ አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። ምሽት 1 ሰዓት ከ15 ላይ ቼልሲ ፖርትቫሌን በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም ያስተናግዳል። ሁለቱ ክለቦች በኤፍኤ ካፕ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ቼልሲ የፕሪሚየር ሊግ፣ ፖርት ቫሌ የፉትቦል ሊግ ዋን (ሶስተኛ ዲቪዚዮን) ክለቦች ናቸው። የምዕራብ ለንደኑ ቼልሲ የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን ስምንት ጊዜ አንስቷል። ፖርት ቫሌ በውድደሩ ትልቁ ውጤቱ ግማሽ ፍጻሜ ከመድረስ የዘለለ አይደለም። 154 ዓመታትን ያስቆጠረው ኤፍኤ ካፕ የዓለማችን አንጋፋ የእግር ኳስ ውድድር ነው።
ምድረ ገነት ሽሬ ከወራጅ ቀጠና ወጥቷል
Apr 3, 2026 251
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ25ኛ ሳምንት መርሐ ግብር መቻል እና ምድረ ገነት ሽሬ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቋል። ማምሻውን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዓለምብርሃን ይግዛው በ50ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል መቻል መሪ ሆኗል። ተካልኝ ዳኜ በ77ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል ለምድረ ገነት ሽሬ አንድ ነጥብ አስገኝቷል። ጨዋታውን ተከትሎ መቻል በ37 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች አላሸነፈም። ምድረ ገነት ሽሬ በ28 ነጥብ ደረጃውን ከ17ኛ ወደ 15ኛ ከፍ በማድረግ ከወራጅ ቀጠና ወጥቷል። ቡድኑ ባለፉት አራት ጨዋታዎች ድል ማስመዝገብ አልቻለም። ዛሬ ቀን ላይ በተካሄዱ ጨዋታዎች በሊጉ ግርጌ የሚገኘው አርባምንጭ ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከባህር ዳር ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ከፋሲል ከነማ ያደረጓቸው ጨዋታዎች ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮ ቴሌኮም ለዲጂታልና ታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ ነው
Apr 3, 2026 354
አዳማ ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም ዘመናዊ የቴሌኮም አገልግሎትን ከማስፋት ባሻገር ለዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ኢትዮ ቴሌኮም በአዳማ ከተማ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከል በመገንባት በዛሬው እለት አገልግሎት አስጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ በኢትዮጵያ የዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአዳማ ከተማ ተገንብቶ በዛሬው እለት ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከልም የዚሁ ልማት ጥረት አካል መሆኑን ጠቁመዋል። የአዳማው ማእከል በአንድ ጊዜ 12 ተሽከርካሪዎችን ቻርጅ የሚያደርግ አቅም እንዳለው ተናግረው በሌሎች አካባቢዎችም የማስፋት እቅድ መኖሩን ገልጸዋል። ኢትዮ ቴሌኮም ከፈጣንና ዘመናዊ የቴሌኮም አገልግሎት በተጨማሪ ለዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም መሰረት አዲስ አበባን ጨምሮ በክልል ከተሞች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጀ ማድረጊያ ማዕከላትን በማስፋፋት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ፤ የስማርት አዳማ ፕሮጀክት ተቀርፆ አሰራርና አገልግሎቶችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ሂደት የኢትዮ ቴሌኮም አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አንስተው በከተማዋ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከል ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል።
በመጪው ሚያዚያ ወር በአብዛኞቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተሻለ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ይኖራል
Apr 3, 2026 69
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ በመጪው ሚያዚያ ወር በአብዛኞቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጠንና ሥርጭት የተሻለ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፤ ከመጋቢት 23 እስከ ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም የበልግ ዝናብ በመጠንና ስርጭት ከፍተኛ ድርሻ የሚወስድበት ወቅት መሆኑን ገልጿል። በዚህም በመጪው ሚያዚያ ወር በአብዛኛዎቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ከቀደሙት ሁለት የበልግ ወራት በመጠንና ሥርጭት የተሻለ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ እንደሚኖር አስታውቋል። ይህም የአየር ጠባይ ሁኔታ የበልግ አብቃይና ተጠቃሚ አካባቢዎች ለሚያከናውኑት የግብርና ሥራ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር ይጠበቃል ብሏል ኢንስቲትዩቱ በመግለጫው። በተለይም በተያዘው የመጋቢት ወር የሚስተዋለው ተከታታይ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ በቡቃያና በተለያየ የዕድገት ደረጃ ላይ ለሚገኙ የበልግ ሰብሎች ምርታማነት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጿል። በደቡብና ደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ የሚጠበቀው እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ለቦረና፣ ጉጂና መሰል ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች ሰብል ልማት፣ ግጦሽ መሬትና የውሃ አቅርቦት ወሳኝ መሆኑንም አመላክቷል። በዚህም የበልግ አብቃይ አካባቢ አርሶና አርብቶ አደሮች ማሳቸውን በማዘጋጀት የሚጠበቀውን አመቺ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ለመጠቀም ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ አሳስቧል። በበልግ ዝናብ መዋዠቅ አዝማሚያ ምክንያት ዝናብ አጠር የሆኑ አካባቢዎች የሚያጋጥማቸውን ተከታታይ ደረቃማ ሁኔታ ለመቋቋም እርጥበትን በማሳ ማቆየት የሚያስችል ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ኢንስቲትዩቱ አስውገንዝቧል። በሌላ በኩል በአንዳንድ አካባቢዎች በሚኖር ከባድ ዝናብ ሊፈጠር ከሚችል የመሬት መንሸራተት፣ የአፈር መሸርሸርና ቅፅበታዊ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭነት ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስቧል።
የክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዜጎችን ተጠቃሚነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው
Apr 3, 2026 76
ባህር ዳር፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በለውጡ ዓመታት የተተገበረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዜጎችን ተጠቃሚነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከእለት ወደ እለት ስኬታማ እየሆነ መምጣቱ እየተመሰከረለት ነው። በመርሃ ግብሩ በብዛትና እና በአይነት መጠነ ሰፊ ችግኞች ተከላ መካሄዱን ለአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፤ ለደን ሽፋን መጨመር ብሎም የምግብ ዋስትን ለማረጋገጥ እያስቻለ ነው። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ መሰሉ ብርሃኑ ለኢዜአ እንዳሉት፤በለውጡ ዓመታት የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዘርፉን ልማት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው። መርሃ ግብሩ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ለውጥ መሻሻል፤ ለደን ሽፋን መጨመር እና የምግብ ዋስትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ መሆኑንም አስረድተዋል። መርሃ ግብሩ ተግባራዊ መደረጉ በክልሉ 13 ነጥብ 9 በመቶ የነበረውን የደን ሽፋን ወደ 18 ነጥብ 9 በመቶ ለማስደግ እንደተቻለም ነው የተናገሩት። በነዚሁ የለውጥ አመታት በ22 ሺህ 189 ተፋሰሶች ላይ በተካሔደው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ምርታማነት ለማሳደግ ያስቻለ መሆኑንም አብራርተዋል። የአረንጓደ ልማቱ በተለይም ለንብ ማነብ፣ ለእንስሳት እርባታና ለፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አንስተዋል።
በአዲስ አበባ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Apr 2, 2026 110
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ሀገር በቀል እና ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና ዘላቂ የአካባቢ ጥበቃን ለማረጋገጥ፣ የለውጡ መንግስት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን በፖሊሲ ደረጃ ቀርጾ ተግባራዊ በማድረጉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ግቡን እውን ማድረግ ችሏል፡፡ በ2018 ዓ.ም ይህንን ሀገራዊ ስኬት ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማከናወን በሀገር አቀፍ ደረጃ 7 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል። ይህንን ግብ ማሳካት የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ። በየካ ክፍለ ከተማ የከተማ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ጽህፈት ቤት የግብአት አቅርቦትና የችግኝ ጣቢያ ባለሙያ የሆኑት ስንታየሁ ግርማ፤ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። በፈረንሳይ የሃ የችግኝ ጣቢያ ለዘንድሮው የክረምት አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚውሉ 150ሺህ የሚሆኑ ሀገር በቀል፣ የውበትና የፍራፍሬ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ እየተዘጋጁ ካሉ የሀገር በቀል የእጽዋት ዝርያዎች መካከል ወይራ እና ብርብራ ተጠቃሽ ሲሆኑ፤ ከፍራፍሬ ዝርያዎች ደግሞ ካዝሚር እና አቮካዶ በስፋት እየተዘጋጁ እንደሚገኙ አብራርተዋል። ይህ የችግኝ ዝግጅት ስራ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚደረገውን ጥረት ከመደገፍ ባለፈ፣ ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ የሚውሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን በማካተት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በጣቢያው ለዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ለተከላ የሚሆኑ የፍራፍሬና ሀገር በቀል ችግኞችን ጨምሮ ሌሎች ዝርያ ያላቸው ችግኞች እያዘጋጁ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሶስኒ ችግኝ ጣቢያ አስተባባሪ አበበች መካ ናቸው። በዚህም በጣቢያው ከ1 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ችግኞች ለማዘጋጀት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ችግኞች ፍሬያማ እንዲሆኑ ጣቢያው ለችግኞች ተገቢውን እንክብካቤ እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ቢሮ የአረንጓዴ ቦታዎች አያያዝ፣ ክትትልና ቁጥጥር ዳይሬክተር ሲሳይ አጥናፉ፤ ለዘንድሮው የክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስድስት ሚሊየን ችግኞችን ለማዘጋጀት ታቅዶ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በመዲናዋ በሚገኙ የችግኝ ጣቢያዎች ለተከላው የሚያስፈልጉ የሀገር በቀል እና የፍራፍሬ ችግኞች በልዩ ትኩረት በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የምታደርገውን ጥረት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ እና ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ሀገርን ለማስተላለፍ የሚያስችል መሠረት የጣለ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 195
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 519
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት። ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው
Mar 22, 2026 208
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
የኢጋድ እና ጃፓን ትብብር መጠናከር ለቀጣናዊ ሰላም የጎላ ሚና አለው
Mar 9, 2026 314
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ጃፓን በቀጣናው ሰላም ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሠሩ ገለጹ። የኢጋድ ምክትል ዋና ፀሐፊ መሐመድ አብዲ ዋሬ ከጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ዳይሬክተር ሂሮኒሪ ሱዙኪ ጋር በጅቡቲ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በኢጋድ ቀጣና ስላለው የሰላም እና ደኅንነት ሁኔታ ሐሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቀጣይም ትብብራቸውን በይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሠሩ ማረጋገጣቸውን ኢጋድ ሴክሬተሪያት መረጃ ጠቁሟል። ጃፓን ለኢጋድ እና አባል ሀገራት፤ በቀጣናው ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት መረጋገጥ ሥራ ዋና አጋር ሆና መቀጠሏም ተመላክቷል።
ሐተታዎች
የጤና ነገር ...
Apr 3, 2026 385
በዮሐንስ ደርበው የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። የኒውትሬሽን ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ የሰው ልጅ የሰውነት ክፍል 60 በመቶው ውኃ እንደመሆኑ ለተስተካከለ ጤና ሚዛን መጠበቅ በቂ ውኃ መጠጣት ይገባል። ውኃን በትክክለኛው መጠንና ጊዜ መውሰድ ከተቻለ የኩላሊት ህመም ተጋላጭነትን 50 በመቶ መቀነስ እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ነገር ግን ሰውነት የሚፈልገውን የውኃ መጠን በአግባቡ ካላገኘ ለዕለታዊ እና በጊዜ ሂደት ሥር ለሚሰድዱ ህመሞች የመጋለጥ ዕድል እንደሚጨምርም ያነሳሉ። ለመሆኑ ሰውነት የሚፈልገውና በቂ የውኃ መጠን የሚባለው መጠኑ ስንት ነው? በቂ ውኃ አለመጠጣትስ የሚያስከትለው ችግር ምንድን ነው? በሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎች ላይ የኒውትሬሽን መምህር፣ ተመራማሪ እና ደራሲ ይሁኔ አየለ ምላሽ አላቸው። አንድ ሰው የሚያስፈልገው የውኃ መጠን በዕድሜ፣ ጾታ፣ በሥራ ባሕርይ፣ በመኖርያ አካባቢ፣ እንደ ጤና ሁኔታው እና እንደ ሰውነት ክብደቱ እንደሚወሰንም በምላሻቸው አስገንዝበዋል። ለምሳሌ የስኳር ታማሚዎች፣ የምታጠባ እናት፣ በዕድሜ የገፉ ሰዎች፣ ብዙ አድካሚና ላብ የሚያወጡ፣ በሞቃታማ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች በቀን 3 ሊትር ውኃ መጠጣት አለባቸው ይላሉ። በአማካይ ግን በቀን አንድ ሰው ከ2 እስከ 3 ሊትር ውኃ መጠጣት እንደሚጠበቅበት ይገልጻሉ። ጤናማ ሕይወት የሚመሠረተው ከውኃ ነው፤ ለምሳሌ ውኃማውን 60 በመቶ የሰውነት ክፍል ሚዛን ለማስጠበቅ የግድ አስፈላጊውን መጠን ውኃ መጠጣት እንደሚገባ ይመክራሉ። በሰውነት ውስጥ የሚካሄደው ሕይወታዊ ሂደት (ባዮሎጂካል ፕሮሰስ) ውኃን መሠረት ያደረገ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለምሳሌ ለተስተካከለ የሥርዓተ-ምግብ ሂደት፣ ቆሻሻን ከሰውነት አጣርቶ ለማስወጣት፣ የአጥንት መገጣጠሚያ ሥራን ለማስተካከል እና ለሌሎችም በርካታ የሰውነት ክፍሎች የተሳለጠ ተግባር ውኃ ቁልፍ መሆኑን አንስተዋል። ይህን ተከትሎም ውኃ ካሎሪ አልባው መድኃኒት (ተፈጥሯዊው መድኃኒት) እስከመባል መድረሱን ነው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ያስረዱት። ሰውነት የሚያስፈልገውን ያህል ውኃ አለመጠጣት ግን ድካም ያስከትላል፤ ለማየት፣ ለመንቀሳቀስ፣ ለመሥራት፣ ለማሰብ፣ ለመረጋጋት . . . አያስችልምና ሲሉ ያብራራሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንድ ሰው ውኃ የመጠማት መጠኑ ከአራት በመቶ በላይ ከሆነ ለሞት ሊጋለጥ እንደሚችልም ጠቅሰዋል። ውኃ አለመጠጣት፤ የጨጓራ ህመምን በማባባስ ማስገሳት፣ የቆዳ ድርቀትና ግርጣት፣ የኩላሊት ህመም ሌሎች የሰውነት ክፍሎችም ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሠሩ ያደርጋል ነው ያሉት። ከምግብ በፊት 30 ደቂቃ ቀድሞ ውኃ መጠጣት ውፍረትን ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በቂ ውኃ ከመጠጣት በተጨማሪ ፍራፍሬዎችንና አትክልቶችን ማዘውተር እንደሚመከርም ገልጸዋል። የፈላ ውኃ እና የዝናብ ውኃን በብዛት መጠጣት በሰውነት ውስጥ ያሉ ንጥረ ነገሮችን በማስወገድና በኩላሊት ላይም ጫና እንደሚፈጥር አመላክተዋል። ለተስተካከለ ጤናማ ሕይወት የግድ ውኃ መጠጣትን ልማድ ማድረግ እንደሚገባም ይመክራሉ። #ውኃ_መጠጣት #ጤና #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency
ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች
Apr 3, 2026 1454
በዮሐንስ ደርበው የለውጡ መንግሥት ኢትዮጵያን ማሥተዳደር ከጀመረ እነሆ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ላይ 8 ዓመት ሞላው። በእነዚህ ዓመታት በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚው፣ በማኅበራዊ ዘርፉ በዲፕሎማሲውና በሌሎችም መስኮች የተለያዩ ስኬቶች ተከናውነዋል። በእነዚህ ጥቂት ዓመታትም ለማሳካት ቀርቶ ለማሳብ የማይደፈሩ ብዙ ውጤቶችም ተመዝግበዋል። የተገኙት ስኬቶች ከጊዜያቸው የፈጠኑ ናቸው። ለዚህም ሕዝቡ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በነቂስ እየወጣ አድናቆቱን ገልጿል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሰጡት የሰላ አመራርነትና ቁርጠኝነትም አክብሮቱንና ምሥጋናውን ገልጿል። የለውጡ መንግሥት አካሄድ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የልማት ፕሮጀክቶችም በይበልጥ ተስፋፍተውና ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መንግሥት ለሚያደርገው ጥረት ከጎኑ እንደሚቆሙም በድጋፍ ሰልፍ ላይ ባስተጋቧቸው መልዕክቶቻቸው አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ በለውጡ መንግሥት ለማሳካት ቀርቶ ለማሰብ የማይደፈሩ ተግባራት ተከናውነዋል። ከእነዚህ ከፍተኛ ጥቅም ከተገኘባቸው የታሪክ እጥፋትን ካሠረጹ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል ጥቂቶቹን ቀጥለን በወፍ በረር እንዳሥሣለን። ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ሥልጣኔ - በምርጫ ካርድ መምረጥ የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። • የኮሪደር ልማት እንደምናውቀው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነትና ልዩ ትኩረት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከሁሉም አስቀድሞ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ ነው። አሁን ላይ ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የበርካታ ከተሞችን ገጽታ የቀየሩ አስደማሚ ሥራዎች ተከናውነውበታል። ይህም በገጠር ጭምር ተጠናክሮ የቀጠለ ጉዳይ ነው። ለዘመናት አሮጌ ገጽታዋን ይዛ ያሸለበችውን አዲስ አበባ እንደ አዲስ የፈጠራትም ይኸው ፕሮጀክት ነው። አሁን ላይ መዲናይቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን ለውጥ ዐይተው ዝም ማለት አልቻሉም። ከመደመማቸው አንጻር የዘወትር አጀንዳቸውም እያደረጓት ይገኛሉ። ይህንን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት፤ ኮሪደር ልማት ማለት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት ነው ማለታቸው ይታወሳል። ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑንንም አስረድተዋል። ከለውጡ መንግሥት ዐበይት የትኩረት መስኮች አንዱ የሆነውን የቱሪዝም ዘርፉን እንቅስቃሴ ለማሳደግም ቁልፍ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ ድርብርብ ፕሮጀክት ነው የኮሪደር ልማት። • የበጋ መስኖ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የለውጡ መንግሥት ዋነኛ ትኩረቱ ነው። ለዚህም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አንዱ ማሳኪያ ሥልት አድርጎ እየተጋ ይገኛል። የበጋ መስኖ ስንዴ ኢትዮጵያ ስንዴን ከውጭ ማስገባት አቁማ መላክ እንድትጀምር ያስቻለ ኢኒሼቲቭ ነው። በዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችና በሜካናይዜሽን ታግዞ በስፋት እየተሠራበትም ይገኛል። ከለውጡ መንግሥት ወዲህ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ምክንያት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በምርታማነት ማደግና የሥራ ዕድል በመፍጠር አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብም ከፍተኛ ውጤት ተገኝቶበታል። ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ ስንዴ ላይ ባሳየችው ትጋት፤ ፍጆታዋን በራሷ ዐቅም የሸፈነችው፣ ስንዴን ከውጭ ማስገባትን ያቆመችው፤ ስንዴን ወደ ውጭ መላክ የጀመረችው በለውጡ መንግሥት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ በመሸለም ለጥረታቸው ዕውቅና መስጠቱም ይታወሳል። • መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀደም ሲል አንድ ጉዳይን ለማስፈጸም እዚያም እዚህም መንከራተት የግድ ነበር። በዚህ አያበቃምና ወረፋውም ሌላ ችግር ነው። መንግሥት በተለያዩ መድረኮች ባካሄዳቸው ሕዝባዊ ውይይቶች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉልን የሚሉ እሮሮዎች በረከቱ። መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል ሥራ ወደ ተግባር አሥገባ። በዚህም መሠረት ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ ጀመረ። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነውም አሉ። ለዚህ ቁርጠኝነታችን አንዱ ማሳያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመራቸውንም ገለጹ። እንግዲህ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ አንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ ታግዘው በተሳለጠ ሂደት እንዲሰጡ በማድረግ የተገልጋይን እንግልት፣ ገንዘብ እና ጊዜ መቀነስ ያስቻለ አሠራር ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት ተደርጎም ይወሰዳል። በየከተሞቹም እየተስፋፋ ነው። • አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ አይ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ተጠቃሚ እንድትሆን ከፍተኛ ጉጉት እንዳላቸው በቁጭት በተለያዩ መድረኮች ያነሳሉ። ለዚህም መፍትሔ ዘይደው ተቋማትን ከማቋቋም ጀምሮ ለዘርፉ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ ተግተዋል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂው ጋር አብሮ ለመጓዝ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን አቋቋመች። የኤ አይ ዩኒቨርሲቲ በመክፈት በግብርናው፣ በጤናው እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠርም በሂደት ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት ቀይሮ ወደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ሕንፃ በተዛወረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአምስት ዓመት ውስጥ አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ መድረሱ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ የሮቦቶችን ሶፍትዌር ብቻ ሳይሆን ውጫዊ የአካል ክፍልን (ሃርድዌር) መሥራት ጀምሯል ብለዋል። ድሮን ማምረት ብቻ ሳይሆን የማነጋገር ዐቅም እየፈጠረ ያለ ተቋም መሆኑንም አንስተዋል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ደረጃ የሚወዳደር አሠራርን የሚከተል መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ምርቶችን አውጥቷል ማለታቸው ይታወቃል። ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮሉሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን ሲሉ ማስገንዘባቸውም ይታወሳል። • የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው። በዚህ ሂደት ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊታአውራሪነት ይጠቀሳል። በተደራጀና ተቋማዊ ሆኖ ባልተቆራረጠ አካሄድ እየተከናወነ ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተተከሉ ችግኞችም በየዘርፉ ተጠቃሚነት አድጓል፤ ተጠናክሮም ይቀጥላል። • የሌማት ትሩፋት ከመጋቢት ሥጦታዎች አንዱ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ነው። የምርት አቅርቦትን በማስፋት ለተረጋጋ ግብይት እና ለተመጣጠነ ሥርዓተ-ምግብ ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከት ላይም ይገኛል። ኢኒሼቲቩ ለግብርና ኢንቨስትመንትና ለሀገራዊ የሥርዓተ-ምግብ መሻሻል ጉልኅ ሚና እየተጫወተ ነው። የዋጋ ንረትን በማረጋጋት፣ የምርት ስብጥርን በማሳደግና በዘላቂነት በማቅረብ ረገድም የጎላ ሚና አለው። የግድ ሰፋፊ መሬት መፈለግ ሳያሻ በትንሽ ቦታ ብዙ በማምረት ፍጆታን ከመሸፈን አልፎ ኢኮኖሚን በመደጎም እና የሥራ ዕድል በመፍጠርም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው። • የቱሪስት መዳረሻ ልማት ቅርሶች እንዲጠገኑ፣ አዳዲስ ሎጂዎች እንዲገነቡ፣ በመዳረሻ ስፍራዎች መሠረተ-ልማት እንዲሟላ ያስቻሉ ተግባራት በለውጡ መንግሥት ተከናውነዋል፤ አሁንም ተጠናክሮ የቀጠለ እና ስኬታማ ኢኒሼቲቭ ነው። በዚህ ሂደት ከሐሳብ አመንጭነት ባሻገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የጻፉትን መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ ጭምር ለቅርስ ጥገናና ለቤተ-መጻሕፍት ግንባታ እንዲውል አድርገዋል። በተጨማሪም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት፤ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ ወደ ተግባር አስገብተዋል። በእነዚህ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። አማራጭ የቱሪስት መዳረሻም ሆነዋል። • የተቋማት ግንባታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል መሪል ሐሳብ በተካሄደው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ፤ የተቋማት ግንባታና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ብለዋል። በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ሲሉም አስገንዝበዋል በወቅቱ። ዘመን የማይለውጣቸው ዘላቂ ጠንካራ ሃገራዊ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ብዙ ርቀት መጓዝም ተችሏል። በመሆኑም የመንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲሆኑ በማድረግ እና ሥርዓት በተለዋወጠ ቁጥር የማይፈርሱ ወይም የሚሻገሩ ተቋማት መገንባት ተችሏል። ይህ ትጋት ተጠናክሮም ቀጥሏል።
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3444
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … በኢዜአ ዐይን …! የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 404
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት
Mar 28, 2026 348
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 13 እስከ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • የ ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን እና የሰው ልጅ ታሪክ በጀመረበት ምድር የተገነባውን ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅት ሎጁ የዛሬ 50 እና 60 ዓመት መሠራት የነበረበት ቢሆንም፤ አሁን ስለዘገየን አንቆጭም ማለታቸው ይታወሳል። ይህን ስለሠራንም አንረካም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሩጫችን ገና ብዙ እንደሆነ፣ አፋር ገና እንዳልተነካ አስበን ይህን ጅማሮ ይበልጥ በማላቅ ለማስቀጠል እንተጋለን ሲሉም ተናግረዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከቃና ቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በኢትዮጵያ ከተሞች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነም ገለጻ አድርገዋል። እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸውን ፋይዳም አንስተዋል። • ኢትዮጵያ በማላቦው ጉባዔ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ ወደ ማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ ያቀኑት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ማላቦ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ማኑዌል ኡሳ ኡዙዌን ጨምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጉባዔው ከመጋቢት 18 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ ሲሆን እስከ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቀጥላል። • የልማት ሥራዎች ጉብኝት በባሕር ዳር እና ጎንደር ከተሞች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የባሕር ዳር ከተማን የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያጎሉና ግንባታቸው እየተፋጠኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የመንገድ መሠረተ-ልማት እና የአየር መንገድ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለኢኮኖሚ ዕድገታችን የጎላ ፋይዳ ይኖራቸዋል ሲሉም በወቅቱ ገልጸዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጎንደርን የውኃ ጥም ይቆርጣል፤ የገበሬውን መሬት ያጠጣል፤ የአካባቢውን ምኅዳር ይለውጣል የተባለው የመገጭ የመጠጥ ውኃ ግድብ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተዋል። በዚሁ ወቅት የሀገር ሀብት ፈስሶባቸው መክነው እና ባክነው የቀሩ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ከሞት እያስነሡ ማፋጠን የዚህ መንግሥት ልዩ መለያው ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም የመገጭ ግድብ ምስክር መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም በጎንደር ከተማ አሥተዳደር ሳይና ሳቢያ የገጠር ቀበሌ የተገነቡ የገጠር ኮሪደር ሞዴል ቤቶችን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅትም በአንድ ወር የግንባታ ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀው ይህ ሞዴል መንደር በአካባቢው ለረጅም ዓመታት የቆየውን የጤና ጣቢያ፣ የመብራትና የውኃ አገልግሎት ጥያቄ በተግባር መልሷል ብለዋል። በሀገራችን ከተማው ብቻ ሳይሆን ገጠሩም እኩል እየተዋበ፣ በልማት እየተገነባና በዕድገት ፍኖት ላይ በጽኑ መሠረት እየተራመደ ይገኛልም ነው ያሉት። ይህ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የማሸጋገር ትልቁ ማሳያችን ነው ሲሉም ገልጸዋል። • "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ በአዲስ አበባ 4ኛው "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም፤ የምንፈልገው ድጋፍን ሳይሆን አጋርነትን ነው፤ እርዳታን ሳይሆን ኢንቨስትመንትን ነው! ለባለ ሀብቶች ምቹ፣ ግልጽና ተራማጅ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ አዘጋጅተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ካፒታል፣ ለችሎታ እና ለዕድል በሯን ወለል አድርጋ መክፈቷንም አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ አሁን በፍጥነት ወደ ከፍታ እየገሠገሠች ባለችበት በዚህ ታሪካዊ የዕድገት ጉዞ፤ ለዓለም አቀፍና ለሀገር ውስጥ ባለ ሀብቶች ኢትዮጵያ ለእናንተ ዝግጁ የሆነ፣ በዕድሎችና በስኬቶች የተሞላ ታላቅ የኢንቨስትመንት መሶብ አላት፤ ኑ አብረን እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል! • የትግራይ ክልል አጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) በሰጡት መግለጫም፤ ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ለመጀመርና ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል። በዚህም ከክልሉ ጊዜያዊ አሥተዳደር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀሌ እና በአዲስ አበባ ከ22 ጊዜ በላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ጥረቶች ውስጥ ሂደቱን በክልሉ ለማካሄድ የሚያስችሉ አስቻይ ሁኔታዎች ባለመፈጠራቸው፤ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተወካዮች ምርጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ እንዲከናወን መወሰኑንም አስረድተዋል።
ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት
Mar 26, 2026 179
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በኋላ የታዛቢነት (Observer) ደረጃን አገኝታለች። እ.ኤ.አ በ2006 የውጭ ንግድ ፖሊሲዋን የሚገልጽ ሰነድ ለድርጅቱ አቅርባለች። ሰነዱ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች፣ የወጪና ገቢ ንግድ ሕጎች፣ የቀረጥ፣ ከቀረጥ ውጭ ያሉ የንግድ ገደቦች፣ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ እና የኢንቨስትመንት ሕጎችን ያካተተ ነበር። በኢትዮጵያ እና በዓለም ንግድ ድርጅት መካከል የመጀመሪያው የድርድር ምዕራፍ የተጀመረው እ.አ.አ በ2008 ነው። ከእ.አ.አ 2008 እስከ 2012 በቆየው የቴክኒክ ድርድር ሶስት የስራ ቡድን ስብስባዎች ተካሂደዋል። በዚህ ወቅት የነበረው ድርድር በዋናነት ኢትዮጵያ ስለ ንግድ ሥርዓቷ ማብራሪያ የምትሰጥባቸው እንጂ፣ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘት አልቻሉም። ከእ.አ.አ 2012 እስከ 2019 የሁለቱ ወገኖች ድርድር ተቋርጦ ነበር፤ ለሰባት ዓመታት እንዲቋረጥ ያደረጉ የተለያዩ ምክንያቶች ይነሳሉ። በወቅቱ ስልጣን የነበረው የኢህአዴግ መንግስት "የገበያ ውድቀት" አለ ብሎ ያምን ነበር። ስለዚህም እንደ ባንክ፣ ቴሌኮም እና ኢነርጂ ያሉ ስትራቴጂካዊ ዘርፎች በመንግስት እጅ መቆየት አለባቸው የሚል አቋም ነበረው። ይህ የመንግስት ጽንሰ ሀሳብ ድርጅቱ የተለያዩ ዘርፎች ለውጭ ክፍት መደረግ አለባቸው ከሚለው አቋም ጋር የሚጣጣም አልነበረም። በዓለም ንግድ ድርጅት የተጠየቁ የንግድ ስርዓትን የማዘመን ስራዎች በሚፈለገው መልኩ አለመሄዳቸውም ለድርድሩ መቆም እንደ ምክንያትነት ይነሳል። የለውጡ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያ የአባልነት ድርድር በድጋሚ ነፍስ ዘርቷል። መንግስት በተለያዩ ዘርፎች የወሰዳቸው ጠንካራ የንግድ እና ኢኮኖሚ እርምጃዎች ድርድሩ በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀጥል አድርጓታል። መንግስት እንደ ቴሌኮም፣ ባንክ እና ሎጅቲክስ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉ በድርጅቱ እንደ ትልቅ ለውጥ የታየ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያን ሕጎች ከድርጅቱ ህጎች ጋር የማጣጣም ስራም ተከናውኗል። ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለው የንግድ ሕግ ማሻሻያ ተደርጎበት ዘመናዊ የንግድ አይነቶች የተካተቱ ሲሆኑ፤ የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መቋቋም የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ላይ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል። ኢትዮጵያ የሸቀጦች ታሪፍ ቅናሽ ሰነዷን አሻሽላ አቅርባለች። ይህም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች የምትጥለው ቀረጥ በምን ያህል መጠንና በስንት ዓመት ውስጥ እንደሚቀንስ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የገባችውን ቃል በተግባር ያሳየችበት ነው። በአሁኑ ሰዓት በዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ኢትዮጵያ በተናጠል እንደ ቻይና፣ ሩሲያ፣ አሜሪካ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችና ካናዳ ካሉ ሀገራት እና ከአውሮፓ ህብረት ጋር የገበያ ተደራሽነት ድርድር እያደረገች ነው። በተደረጉት የተናጥል ድርድሮች ላይም ለኢትዮጵያ አባልነት ሙሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። ከአዕምሯዊ ንብረት ጋር በተያያዘ የፈጠራ ውጤቶችን፣ የንግድ ምልክቶችን እና የባህል እሴቶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ጠንካራ ሕግና ተቋም መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጓል። የጉምሩክ አሰራር የሸቀጦችን ፍሰት ለማሳለጥ የዲጂታል ጉምሩክ አሰራርን የማስፋፋት ስራ በመንግስት በኩል ተከናውኗል። 14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የሚኒስትሮች ስብስባ ከመጋቢት 17 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በካሜሮን ያውንዴ መካሄድ ጀምሯል። በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክም በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ያውንዴ ገብቷል። ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከስብስባው ጎን ለጎን የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን ሚኒስትሩ ከዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላ (ዶ/ር) ጋር ያደረጉት ውይይትም በዋናነት የሚጠቀስ ነው። በውይይቱ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለድርጅቱ አባል አገራት ከ1200 በላይ ለሚሆኑ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠቷንና ከ419 በላይ የሕግና የፖሊሲ ይዘቶችን ማሳወቋን ጠቁመዋል። የያውንዴው ስብስባ ለኢትዮጵያ የአባልነት ጉዞ የፖለቲካ ድጋፍን ለማሰባሰብ ያስችላታል። በቅርቡ የድርጅቱ አባል ከሆኑ የአፍሪካ እና ሌሎች ሀገራት ጋር የቴክኒክ እና የተሞክሮ ልውውጥ ለማድረግም ምቹ አጋጣሚ ይፈጥርላታል። የያውንዴው ውይይት ኢትዮጵያ በቴክኒክ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በፖለቲካ ደረጃም ለድርድር ዝግጁ መሆኗን የምታሳይበት ነው። የዓለም የንግድ ድርጅት እ.አ.አ በ1995 የተቋቋመ ሲሆን ዋና መቀመጫው ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ነው።ድርጅቱ 166 አባል ሀገራት አሉት። አባል ሀገራቱ የዓለምን 98 በመቶ የንግድ ልውውጥን እንደሚሸፍኑ መረጃዎች ያመለክታሉ። የዓለም ንግድ ድርጅት በዓለም ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው አቅምና ተጽዕኖ እጅግ ከፍተኛ ነው። ድርጅቱ ራሱ ገንዘብ የሚያበድር ባንክ ባይሆንም፣ የዓለምን የንግድ “የጨዋታ ሕግ" በመቅረጽ ረገድ ያለው ሚና ትልቅ መሆኑን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል መሆኗ የገበያ እድሏ እንዲሰፋ ያደርጋል። የኢትዮጵያ ምርቶች በ160+ አባል አገራት ገበያ ውስጥ ያለ አድሎና በዝቅተኛ ታሪፍ እንዲገቡ ዕድል ይሰጣል። ይህ በተለይም ለግብርና ውጤቶችና ለጨርቃጨርቅ ምርቶች ትልቅ በር ይከፍታል። የኢትዮጵያ አባል መሆን ሀገሪቷ ዓለም አቀፍ የንግድ ሕጎችን እንደምታከብር ማረጋገጫ ስለሚሆን፤ ትልልቅ የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ላይ ያላቸው እምነት እንዲጨምር ያደርጋል። ኢትዮጵያ አባል መሆኗ ከሌሎች አገራት ጋር የንግድ አለመግባባቶች ቢገጥሟት፣ በድርጅቱ የክርክር መፍቻ መድረክ አማካኝነት መብቷን ማስከበር ትችላለች። ኢትዮጵያ የንግድ አቅሟን ለመገንባት የሚያግዙ ልዩ ልዩ ሥልጠናዎችንና የቴክኒክ ድጋፎችን ከድርጅቱ ማግኘት ትችላለች። ኢትዮጵያ በያዘችው ፍጥነት እና ቁርጠኝነት ከቀጠለች እ.አ.አ 2026 የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድሯን የማጠናቀቅ እድሏ ሰፊ ነው። የድርድሩ መጠናቀቅ ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማጽደቅ እና የአገር ውስጥ ህጎችን ከድርጅቱ ሕግ ጋር የማጣጣም ስራዎችን ጨምሮ በቀጣይ ምዕራፍ ለሚከናወኑ ስራዎች በር ይከፍታል። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን ውጥኗ ከ23 ዓመታት በኋላ እውን ሊሆን የተቃረበ ሲሆን ድርድሩም ወደ መደምደሚያው ምዕራፍ ደርሷል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 21, 2026 854
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 6 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ማሳሰቢያ በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ስለዚህ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በኃላፊነት ልንጠቀም ይገባል ሲሉ ያሳሰቡት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ባሳለፍነው ሳምንት … ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል የነዳጅ ብክነትን ለመቀነስ ምን ዓይነት ብልኀት መጠቀም ይመከራል? ፕሬዚዳንት ታዬ ያስጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባሳለፍነው ሳምንት የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑን ገልጸው፤ የሕይወት ምሉዕነት የሚረጋገጠው ካለው ላይ ቆርሶ በመስጠት መሆኑን አስገንዝበዋል። ለተቸገሩ መድረስና ለወገን መቆም ትልቅ የመንፈስ ዕርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ መጠናከር እንዳለበትም አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ የተወያዩት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጉብኝት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በእንዶዴ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ እና በኤ ኤም ጂ (AMG) - እንዶዴ የባቡር መሥመር ፕሮጀክቶች ላይ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። እነዚህ በራስ ዐቅም የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነታችንን ከማሻሻል ባለፈ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ያጸናሉ ሲሉም በዚሁ ወቅት በአጽንዖት ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ጋር በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ መሥተዳድሮች፣ ከከተማ አሥተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ሥርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ሥርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1 ሺህ 452 ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሐሴ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ረመዳን ወር ተጠናቅቆ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት የተከበረው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ለበዓሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች የፌደራል፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። #ባሳለፍነው_ሣምንት #ኢዜአ
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 21, 2026 299
በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ (በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት ስትወጥን የቀደመ ወረቷን፤ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶቿን ይዛ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን ቀረጸች። ይህን ዕውን ለማድረግ ስትዘይድም የሕዝቧን የፋይናንስ፣ የዕውቀት እና የጉልበት ዐቅም በመደመር መጠቀምን ሻተች። በዚህም መሠረት በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶችን አስመዘገበች። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። በኢዜአ ዐይን …! ✍️ ገበታ ለሸገር በአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻዎችና መናፈሻዎችን ለማልማት በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረገው ገበታ ለሸገር ኢኒሼቲቭ፤ ከእንጦጦ ተራራ እስከ አቃቂ ወንዝ ያለውን የሚሸፍን ነው። የሚሠራበትን ገንዘብ ለማሰባሰብም የገበታ ለሸገር የእራት ምሽት በዳግማዊ አጼ ምኒልክ የግብር አዳራሽ ተዘጋጀ፤ ባለሀብቶች፣ የንግድ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ጨምሮ ዓለም አቀፍና አኅጉራዊ ድርጅቶችም ተሳትፈዋል። ኢኒሼቲቩ አንድነት ፓርክን ጨምሮ የእንጦጦ መናፈሻንና ሌሎች የተለያዩ መዲናዋን ያስዋቡ በረከቶችን ችሯል። ይህም የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት በርካታ ቱሪስቶችን ከመሳብ ባለፈ፤ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለምጣኔ ሃብት ዕድገት ጉልኅ አስተዋጽዖ አበርክቷል። ለዚህ ሁሉ ስኬት መነሻ የሆኑትን ጉዳዮች ያስጀመሩትም ያስፈጸሙትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በገበታ ለሸገር የተገኙ ውጤቶችን መነሻ በማድረግ ገበታ ለሀገር የተሰኘውን ኢኒሼቲቭ አበሠሩ። ✍️ ገበታ ለሀገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነሐሴ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻን ለማልማት ያለመ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አዘጋጅተዋል። ይህም በአዲስ አበባ ከተሠራው ገበታ ለሸገር ቀጥሎ የተከናወነ ነው። በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የገበታ ለሀገር ዓላማ የተለያዩ አካላትን በማሳተፍ የቱሪስት መስኅብ የሚሆኑና የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ አካባቢዎችን ማዘጋጀት መሆኑን አስገንዝበዋል። በገበታ ለሀገር መርሐ-ግብር ባለሀብቶችን ጨምሮ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ 3 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህን ለማሳካት የሀገሪቱን ባለሃብቶች፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች በተለያዩ መርሐ-ግብሮች የተሳተፉበት የገቢ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ውጤታማ ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገበታ ለሀገር ውጥን፤ እንደ ሀላላ ኬላ፣ ጨበራ ጩርጩራ፣ ወንጪ እና ጎርጎራ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና የተፈጥሮ ሀብቶችን አጉልተው በማሳየት ይበል ያሰኘ ውጤት አስመዝግቧል። ✍️ ገበታ ለትውልድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2015 ዓ.ም ገበታ ለትውልድ የተሰኘ ኢኒሼቲቭ ይፋ ያደረጉ ሲሆን፤ ይህም ተጨማሪ መዳረሻዎች እንዲለሙ አስችሏል። በዚህ ኢኒሼቲቭ ሥር በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በአፋርና ሶማሌ ክልሎች የመዳረሻ ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል፤ እየተከናወኑም ነው። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዳሴ ግድብ አካባቢና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የፕሮጀክቱ አካል የሆኑ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራዎች እየለሙ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውን የሸበሌ ሪዞርት በይፋ መርቀዋል። እያንዳንዱ የሪዞርቱ ገጽታ የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ባህላዊ ሐብት የሚያንፀባርቅ ነው። ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በሚደረገው ጉዞ ትልቅ ታሪካዊ እጥፋት እንደሆነም ተገልጿል። ሎጎ ሐይቅ ሪዞርትም ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመረቀ ሲሆን፤ ለጎብኚዎች የማይረሳ ትውስታን የሚሰጥ እጅግ ማራኪ ቦታ ሆኖ ቀርቧል። ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለመሆን ያላትን ቁርጠኝነትና ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ቋሚ ምስክርም ነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት። የቱሪዝም ልማቱን ከተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ፣ ከዘላቂነትና ከአካታችነት ጋር በማቀናጀት፤ ሪዞርቱ የወሎ ሕዝብ ያለውን ጥልቅ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ዕሴት ለዓለም ማኅበረሰብ የሚያስተዋውቅበት ሰፊ ገበታ ሆኖ ያገለግላል። ታሪካዊ ቦታዎችና የሀገር መገለጫ መሠረተ-ልማቶች ብሔራዊ ትርክቶችንም የሚገነቡ ናቸው። በአጠቃላይ እነዚህ ሁሉ ጥረቶች ለአካባቢ ጥበቃ ቅድሚያ በመስጠት ብሎም በየአካባቢው የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል። የቱሪዝም ዘርፉን ለማጎልበት፣ ብዙ ጎብኚዎችን ለመሳብ፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማጠናከር፣ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው። እንዲሁም ነባር ቅርሶችን በማደስና በመጠገን ለትውልድ ለማሻገር ደማቅ ዐሻራ አሳርፈዋል። በሌላ በኩል የቱሪዝም መዳረሻዎችን ማልማት የመንግሥት ብቻ እንዳልሆነ ዐሳይተዋል። ባለሀብቶችና ሌሎች የማኅበረሰብ ክፍሎችም ሀገራቸውን የመሥራት ሚና እንደሚጠበቅባቸው አሥተምረዋል። ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት ብሎም በርካታ የሥራ ዕድሎች በመፍጠር በኢኮኖሚው ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በኢትዮጵያም ቱሪዝም መንግሥት ላስጀመረው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የማዕዘን ድንጋይ ነው። ከአምስቱ ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎችም አንዱ የሆነው ለዚህ ነው። መሠረተ-ልማቶች ከሚገነቡባቸው ጡቦች ባለፈ የነገን ሀገራዊ ማንነት፣ ራዕይ እና መዳረሻን ይበይናሉ። ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ እንኳንም ታሰቡ፤ እንኳንም ተሳኩ። ይህ ባይሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ተጨማሪ መዳረሻ ባላገኘች ነበር።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3798
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2568
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8356
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6845
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የጀጎል አለም አቀፍ ቅርስን የታደገው ሀገራዊ ለውጥ
Apr 4, 2026 200
የስልጣኔ መነሻ የጥበብ መፍለቂያ የሆነችው የምስራቋ ፈርጥ ሀረር የንግድ፣ የፖለቲካና ማህበራዊ ትስስር ማዕከል ሆና በትውልድ ቅብብሎሽ ከአንድ ሺህ አመታት በላይ የተሻገረች እድሜ ጠገብ ከተማ ነች። በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በምስራቅ አፍሪካ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርትና የንግድ ማዕከል የነበረችው ከተማዋ በርካታ ቋሚና ተንቀሳቃሽ እንዲሁም የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቁሳዊና ሀይማኖታዊ ቅርሶችን የያዘች ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ ነች። ከእነዚህ ቅርሶች መካከል ጥንታዊ የስነ-ህንፃ የጥበብ፣ የከተማ ፕላን፣ ባህላዊ የመሬት አጠቃቀም፤ አካባቢያዊ መስተጋብርና የስልጠኔ መገለጫ በሚል እኤአ በ2006 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም ዩኔስኮ በአለም አቀፍ ቅርስነት የተመዘገበው የጀጎል ቅርስ ይጠቀሳል፡፡ ቅርሱ ምንም እንኳን በኪነ ህንፃ ጥበብ በላቁ በአርቆ አሳቢ አባቶች እንዳይፈርስና ሚዛኑን ጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ በተመረጠ ድንጋይ እና አፈር በልዩ ጥበብ የተገነባ ቢሆንም በጥበቃና እንክብካቤ ጉድለት ምክንያት ከግማሽ ምዕተ አመታት በላይ እድሜን ባስቆጠረው ቅርስ ላይ አደጋ ተጋርጦበት ቆይቷል። በቅርሱ ውስጣዊ እና ውጫዊ ክፍሎች የህገ-ወጥ ግንባታዎች መበራከትና በሌሎች ምክንያቶች በደረሰበት ጉዳት የጥንት ስልጣኔ ምልክት የሆነው አለም አቀፉ የጀጎል ቅርስ ከዩኔስኮ የአለም ቅርስነት እስከመሰረዝ የደረሰ አደጋ ተደቅኖበት ነበር። ሆኖም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በአዲስ እሳቤ፤ በተደመረ አቅምና በላቀ ቁርጠኝነት፤ ህዝብን በማሳተፍ ከመንግስት ምንም አይነት በጀት ሳይመደብለት ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ማልማት ተቻለ። አሁን ላይ እነኛ በሸራና በጨርቅ በተሰሩ ህገወጥ ግንባታዎች ተወሮ የነበረው 3ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የጀጎል ግንብ ዙሪያ በአበቦችና ቅርሱን በሚያስውቡ ስራዎች ደምቀዋል። በዚህም አባቶች ከዘመኑ ቀድመው ዛሬም ድረስ ግርምትን በሚያጭር ጥበብ አንፀው ያኖሩት ይህንን የሀገር ሀብት በመታደግ ትውልዱን ከታሪክ ተወቃሽነት ወደ ዳግም ታሪክ ሰሪነት እንዲሸጋገር ማድረግ ተችሏል። ስራውም የትላንትን መሰረት ሳያናጋ፤ የቀድሞ አባቶችን ጥበብና ስልጣኔ ሳይጋፋና ሳይዘነጋ ጥንታዊውን ከዘመናዊ ጋር አዋህዶ ቅርስ መገኛ ለሆኑ ሌሎች አካባቢዎችም ተምሳሌት በሚሆን ደረጃ አስደናቂ ስራ ተከናወነ። የአካባቢውን ሀብትና እውቀት በመጠቀም እውን የተደረገው ይህ ስራ በእያንዳንዱ የሀረሪ ጥንታዊ ቤቶች በሚገኙ የታሪክ አሻራዎችና የባህል መገለጫዎች እንዲደምቅም ሆኗል። ይህ ትውልድ ተሻጋሪ ስራ ቅርሱን ከአደጋ ከመታደግ ባለፈ ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከግለሰብ እስከ ማህበራትና የዳያስፖራ አባላት ድረስ ሁሉም በያገባኛል ስሜት አሻራውን ያኖረበት ዘመን ተሻጋሪ ፕሮጀክት ነው። ይህም በቅርሱ ላይ የእኔነት ስሜት እንዲጎለብት በማድረግ የእይታ ለውጥ እንዲመጣ ያስቻለና ቀደም ሲል የነበሩ የግለኝነት አስተሳሰቦችን በመቅረፍ የወል እሳቤ እውን የሆነበት ፕሮጀክት ሆኖ ታይቷል። ዛሬ ላይ እነኛ የቆሻሻ መጣያ የነበሩ እና በአካባቢው ለማለፍ ከባድ የነበሩ የጀጎል መንገዶች ፀድተው ውብ ሆነዋል። ይዘታቸውን ለቀው የነበሩ ቅርሶችም የአለም ቅርስነት ክብርና መስፈርትን በሚመጥን ደረጃ ታድሰዋል። ዛሬ የጀጎል ነዋሪ እንደቀድሞ አካባቢውን ለቆ ለመሄድ ሳይሆን መኖርን የሚመርጥባት የወጣውም መመለስን የሚመኝባት ምቹ አካባቢ ሆናለች። የመቻል ምልክት የትብብር ውጤትና የአብሮነት ጉልበት በተግባር የታየበት የጁገል መልሶ ልማት ጥንታውን መንደር ለነዋሪዎች ምቹ ለጎብኚዎች ተመራጭ የጉብኝት ስፍራ እንዲሆን ማድረግ ተችሏል። በለውጡ መንግስት በአዲስ መልክና ቀለም የተዋበው ጀጎል የሀረርን ቀደምት ስልጣኔ እየመሰከረ የሀገርንም ገፅታ እየገነባ ይገኛል።
የለውጡ ትሩፋት - ግብርናን የሚያሻግረው ዕይታ
Apr 3, 2026 85
የለውጡ ትሩፋት - ግብርናን የሚያሻግረው ዕይታ በአሸናፊ በድዬ በኢትዮጵያ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ልዩ ቀን ሆኖ በታሪክ ተመዝግቧል። ዕለቱ አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበትና ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ የተጀመረበት ነው። ኢትዮጵያ ከለውጡ በኋላ በፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች መሠረታዊ ውጤቶችን እያስመዘገበችም ትገኛለች። በተለይ በሀገር አቀፍ የኢኮኖሚ ሪፎርም መሰረት ፈጣን፣ አስተማማኝና ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል። ለዚህም ነው ዕድገቱን ፈጣንና ተከታታይ ለማድረግ አምስት ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ተለይተው ወደ ሥራ የተገባው። እነዚህ ዘርፎች ኢኮኖሚው በአንድ ዘርፍ ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ እንዳይቀርና በማንኛውም ዓለም አቀፋዊ ጫና ውስጥ የማይናወጥ ጽኑ መሠረት እንዲኖረው ያደርጋል። በተለይም ግብርናው ለኢንዱስትሪው ግብዓት ሲያቀርብ፣ ቴክኖሎጂው ደግሞ የግብርናውን ምርታማነት ሲያሳልጥ፣ ማዕድንና ቱሪዝም ደግሞ ለሌሎች ዘርፎች መስፋፋት ወሳኝ የሆነውን የውጭ ምንዛሬ ሲያመነጭ የተቀናጀ የሰንሰለት አሰራር መዘርጋት ይችላል። በዚህ መሠረት፣ ከለወጡ ወዲህ የሀገሪቷን የኢኮኖሚ ገጽታ እየቀየሩ ያሉትን እነዚህን ዘርፎችና የታሪካዊ ቀኗን ትሩፋት በወፍ በረር እንመለከታለን። 1. ግብርና ፦ የስንዴ አብዮት ግብርናው አሁንም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው። ከለውጥ ማግስት በኋላ ከዝናብ ጥገኝነት በመውጣትና በቴክኖሎጂ በመታገዝ በዘርፉ ታሪክ ቀያሪ ስኬት እየተመዘገበ ይገኛል። የዚህ ስኬት ዋነኛ ማሳያ ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ አድናቆትን ያተረፈው የኢትዮጵያ የስንዴ አብዮት ነው። 👉የቀድሞ ቅኝት፦ የዳራ እውነታዎችና የጥገኝነት ቀንበር ከሀገራዊ ለውጡ በፊት የኢትዮጵያ ግብርና ገጽታ በእድገት ማነቆዎች የተጠፈረ ነበር። ኢትዮጵያ ሰፊ ለም መሬት፣ አመቺ የአየር ንብረትና ብዙ የሰው ኃይል እያላት ለዓመታዊ የፍጆታ ፍላጎቷ የሚሆን በቂ ስንዴ ማምረት አቅቷት ለዓመታት ቆይታለች። በዚህም ምክንያት በየዓመቱ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ በሚደርስ የውጭ ምንዛሬ ስንዴ በመግዛት ከውጭ ለማስገባት ትገደድ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ታሪኳ ነው። የዚህ ዓይነቱ አካሄድ ኢትዮጵያ የማምረት አቅም እያላት ለውጪ ምንዛሪ ወጪ ዳርጓት ቆይቷል፤ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ የሚፈጠሩ የዋጋ መዋዠቆችና ጂኦ-ፖለቲካዊ ቀውሶች ተጋለጭነቷን አስፍቶት እንደነበር የሚታይ እውነት ነው። 👉የለውጡ ስትራቴጂና ቁርጠኝነት የስኬት ጅማሮ ይህ ቢያንስ በስንዴ ጥገኛ አድርጎን የቆየው ተግዳሮት ታሪክ በሚቀይር መልኩ አዲስ ምዕራፍ ያስከፈተው መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው ሀገራዊ ለውጥ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነትና ያላሰለሰ ክትትል የተጀመረው የተቀናጀ ጥረት የኢትዮጵያን ግብርና ከነበረበት ተግዳሮት አላቆ ዘመናዊና ውጤታማ ምዕራፍ ያሸጋገረው ጉዞ ጀምሯል። ለዚህ በአብነት የሚጠቀሰው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ስትራቴጂ ነው። በ2011 ዓ.ም በሙከራ ደረጃ በ3 ሺህ 500 ሄክታር መሬት ላይ ብቻ የተጀመረው የመስኖ ስንዴ ልማት፣ ዘንድሮ አራት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሄክታር ደርሷል፡፡ የምርት መጠኑም ከ100 ሺህ ኩንታል ወደ 175 ሚሊዮን ኩንታል ከፍ ብሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት በመኸር፣ በበልግና በመስኖ የሚለማው መሬት ስፋት ከሀገራዊ ለውጡ በፊት ካለው ጋር ሲነጻጸር እምርታዊ ለውጥ ማሳየቱን ማስተዋል ይቻላል። በዚህም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች ሆናለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ዓመት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በኢኮኖሚው ዘርፍ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ኢትዮጵያ በአፍሪካ አንደኛ ስንዴ አምራች ሀገር መሆኗን መግለጻቸውን ይታወሳል። ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ የጀመረችው ስትራቴጂያዊ ንቅናቄ በሀገሪቷ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የምርት ዕድገት አስመዝግቧል። ይህም የዘርፉን ጉዞ ከነበረበት ዝቅተኛ ደረጃ አላቆ በአጭር ጊዜ ውስጥ በብዙ እጥፍ እንዲልቅና ለሀገራዊ የምግብ ሉዓላዊነት ዋነኛ መሰረት እንዲሆን አስችሎታል። 👉የምግብ ሉዓላዊነትና የሀገር ክብር ዛሬ ኢትዮጵያ ስንዴን ከውጭ ከማስገባት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን፣ ስንዴ ለውጭ ገበያ መላክ የጀመረችበት አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ይህም የለወጡ ትሩፋት ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬን በማዳን፣ በዓለም አቀፍ መድረክ የኢትዮጵያን ተደራዳሪነትና ክብር ከፍ አድርጓል። በተጨማሪም እንደ አረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋትና መሰል መርሃ-ግብሮች በዘርፉ እምርታዊ ለውጥ እያመጡ ይገኛሉ። 2. ኢንዱስትሪ የኢንዱስትሪው ዘርፍ በተለይም አምራች ኢንዱስትሪው ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ወዲህ የሀገር ውስጥ ምርትን በመተካትና ለውጭ ገበያ የሚሆን ጥራት ያለው ምርት በማቅረብ ላይ ያተኮረ ነው። በ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ አማካኝነት ከዚህ ቀደም ተዘግተው የነበሩ በርካታ ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ተመልሰዋል። የኮንስትራክሽን ግብዓቶችን (እንደ ሲሚንቶና ብረት) በሀገር ውስጥ የማምረት አቅም በማደጉ የግንባታ ዘርፉን አነቃቅቷል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመነትን በመሳብ ለሺዎች የሥራ ዕድል ፈጥረዋል። 3. ማዕድን ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት በሳይንሳዊ መንገድ በመጠቀም የውጭ ምንዛሬ ግኝቷን ለማሳደግ ከለውጡ ወዲህ ትልቅ ርብርብ እየተደረገ ነው። የወርቅ፣ የድንጋይ ከሰልና የሌሎች ማዕድናት ምርት በከፍተኛ ሁኔታ አድጓል። በተለይ የድንጋይ ከሰልን በሀገር ውስጥ ማምረት መቻሉ ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚወጣውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ቀንሷል። በዘርፉ ሕገ-ወጥ ዝውውርን በመቆጣጠርና ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት የመንግሥት ገቢ እንዲያድግ ተደርጓል። 4. ቱሪዝም ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ወዲህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመጪነትና ተግባራዊ ስራዎች ቱሪዝም በአዲስ መልክ የተወለደና ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ዘርፍ ሆኗል። ቀደም ሲል በታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶች ላይ ብቻ ተወስኖ የቆየው እንቅስቃሴ፣ አሁን ላይ ሰው ሰራሽ መስህቦችን በማካተት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን አረጋግጧል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተገነቡት አንድነት፣ እንጦጦና ወዳጅነት ፓርኮች የአዲስ አበባን ገጽታ ሙሉ በሙሉ ከመቀየራቸውም በላይ ለከተማ ቱሪዝም አዲስ ምዕራፍ ከፍተዋል። በ"ገበታ ለሀገር" መርሃ-ግብር የተገነቡትና በቅርቡ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት የሆኑት እንደ ወንጪ (Eco-Tourism)፣ ጎርጎራ ያሉ መዳረሻዎች የሀገሪቷን የቱሪዝም ሀብት ወደ ክልሎች በማስፋፋት ረገድ ትልቅ ስኬት አስመዝግበዋል። በቅርቡ ተመርቆ ወደ ሥራ የገባው የታላቁ ቤተ-መንግሥት የቱሪስት መዳረሻ እና በ"ገበታ ለትውልድ" ስር እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶች ዘርፉን ይበልጥ አጠናክረውታል። አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲና በመሆኗ፣ በትላልቅ ስብሰባዎች አማካኝነት የሚገኘው ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ አድጓል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ያስታወቁት፤ አዲስ አበባን የቱሪዝም ኮንፍረንስ ማዕከል ለማድረግ የተከናወኑ በርካታ የልማት ሥራዎችና ሜጋ ፕሮጀክቶች ፍሬ ማፍራት በመጀመራቸው፣ በከተማዋ የሚካሄዱ ኩነቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ነው። በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ብቻ 150 የሚሆኑ አህጉር አቀፍና ዓለም አቀፍ ኹነቶች በአዲስ አበባ የተካሄዱ ሲሆን፤ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ50 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን መግለጻቸው ይታወቃል። ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር የቱሪስት ፍሰት ጋር ተያይዞ ባለፉት ስድስት ወራት 155 ቢሊየን ብር ወደ ኢኮኖሚው ፈሰስ መደረጉን የገለጹ ሲሆን፤ መዲናዋን የቱሪዝም ኮንፍረንስ ማዕከል ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ለኹነቶቹ መጨመር በተጨባጭ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ናቸው ብለዋል። የአዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በክልሎች ከተሞች እየተሰሩ ያሉት የኮሪደር ልማቶች ከተማዎቹን ልዩና ውብ ከማድረጋቸው ባሻገር ለቱሪስት መስህብ ሆነዋል። 5. ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ/ዲጂታል ኢኮኖሚ ይህ ዘርፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመደገፍ ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ የሚያደርግ ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ለውጥ ወዲህ የደመቀ የለውጥ ሞተር ነው። የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" ስኬቶች በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶች (ፓስፖርት፣ ንግድ ፈቃድና ታክስ ክፍያ) በበይነ-መረብ በመሆናቸው ሌብነትንና እንግልትን ይቀንሳሉ። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች በ"ፋይዳ" መታወቂያ የታቀፉ ሲሆን፤ በ"ቴሌ ብር"ና መሰል አማራጮች የገንዘብ ዝውውር መዘመን ችሏል። የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ወደ ሥራ መግባት የአገልግሎት ጥራትንና ተደራሽነትን ጨምሯል። የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ራዕይ የ2025 ስኬትን መሠረት በማድረግ አሁን ላይ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን (AI) በስፋት የመጠቀም ግብ ወዳለው ቀጣይ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። በ"ኢትዮ-ኮደሮች" መርሃ-ግብር አምስት ሚሊዮን ወጣቶችን በዲጂታል ክህሎት ለማሰልጠን እየተሠራ ያለው ሥራ ወጣቶችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እያደረገም ይገኛል። እነዚህ አምስት ምሰሶዎች ተነጣጥለው የሚታዩ ሳይሆን አንዱ ሌላውን የሚደግፉ ናቸው። ይህ ታሪካዊ ለውጥ ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሸጋግር ስትራቴጂ ነው። የነገዋ ኢትዮጵያ በራሷ የምትመገብና ለሌሎችም የምትተርፍ ጠንካራ ሀገር መሆኗን ያረጋገጠ ታርካዊ ክንውን ነው።