ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ከሻዕቢያ መንግስት ጋር በማበር የሚመለስ የትግራይ ህዝብ ጥያቄ የለም - የትግራይ ተወላጆች
Feb 14, 2026 65
‎አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡- ከሻዕቢያ መንግስት ጋር በማበር የሚመለስ አንዳች የሰላምና የልማት ጥያቄ የለም ሲሉ የትግራይ ተወላጆች ገለጹ፡፡ ለትግራይ ክልል ብሎም ለኢትዮጵያ ህዝብ ከሻዕቢያ በላይ ጠላት የለም በማለት ነው የገለጹት። የፌዴራል መንግስት በህገ መንግስቱና በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት በትግራይ ክልል ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ ነውም ብለዋል።   የትግራይ ለውጥ ፈላጊዎች ንቅናቄ "ሰላም ለህዝባችን፣ ለውጥ ለወደፊት ተስፋችን” በሚል መሪ ሃሳብ ከክልሉ ተወላጆች ጋር በአዲስ አበባ ምክክር አድርጓል፡፡ የትግራይ የለውጥ ፈላጊዎች ንቅናቄ አባልና የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተደራዳሪ አሰፋ አብርሃ በዚህ ወቅት፤ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ለመፍታት የተፈረመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ ተፈጻሚ አለመሆኑን ጠቅሰዋል። በተለይም ጥቂት የቀድሞ ህወሓት አንጃዎች የኢትዮጵያና የትግራይ ህዝብ ጠላት ከሆነው የሻዕቢያ መንግስት ጋር ተሰልፈው የኢፌዴሪ ህገ መንግስትና የፕሪቶሪያን ስምምነት መጣሳቸውን ተናግረዋል፡፡ ለትግራይ ክልል ብሎም ለኢትዮጵያ ህዝብ ከሻዕቢያ በላይ ጠላት የለም ያሉት አቶ አሰፋ፤ ከሻዕቢያ ኃይል ጋር መሰለፍ ባንዳነት መሆኑን አስረድተዋል። የትግራይ ህዝብ ከሁለተኛ ጥፋት ለመዳን ጦርነትን በመቃወምና በሰላማዊ መንገድ በመታገል ከኋላቀሩ አንጃ መላቀቅ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በትግራይ ክልል ምርጫ ተካሂዶ መደበኛና ህጋዊ መንግስት እንዲኖር መስራት የንቅናቄያቸው ዓላማ መሆኑን በመጥቀስ፤ ከፌዴራል መንግስት ጋር አብሮ መስራት ሀገራዊ ግዴታችን ነው ብለዋል፡፡ የትግራይ የለውጥ ፈላጊዎች ንቅናቄ አባል ሌተናል ጀኔራል ፃድቃን ወልደትንሳኤ፤ የፌዴራል መንግስት ተፈናቃዮችን በመመለስ ከመጀመሪያው ጀምሮ እንቅፋት ሆኖ እንደማያውቅ ገልጸዋል፡፡ የትግራይ የፖለቲካ ችግሮች በሂደት እንዲፈቱና ቅድሚያ ለተፈናቃዮችና ሰብዓዊ ድጋፍ የሚል ስምምነት እንደነበርም አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ የቀድሞ ህወሓት አንጃ የራሱን ፍላጎት ለማሳካት ተፈናቃዮችን እንዳይመለሱ በማድረግ የፖለቲካ መያዣ አድርጓቸዋል ብለዋል፡፡ የፌዴራል መንግስት በህገ መንግስቱና በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት በትግራይ ክልል ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።   የቀድሞው ህወሓት ከሻዕቢያ መንግስትና ሌሎች ፀረ ሰላም ሃይሎች ጋር በመቀናጀት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ጥሶ ለጦርነት እየተዘጋጀ መሆኑንም ሌተናል ጀኔራል ጻድቃን አንስተዋል፡፡ የትግራይ ክልል ችግር የሚፈታው በሰላማዊ መንገድና ከፌዴራል መንግስት ጋር በመተባበር መሆኑንም ጠቅሰዋል። ከሻዕቢያ ጋር በመተባበርና በጦርነት የሚፈታም ሆነ የሚሳካ ጉዳይ እንደሌለ በመግለጽ፤ የትግራይ ህዝብ በየአካባቢው ተደራጅቶ ባንዳና ባዳን መታገል አለበት ብለዋል፡፡   የባይቶና ፓርቲ ሃላፊ ክብሮም በርኸ በበኩላቸው፤ የቀድሞ ህወሓት የትግራይን ህዝብ ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ ስቃዩን ለማብዛት ከሻዕቢያ ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እነዚህ አካላት ከውጭ ጠላት ጋር በማበር ጦርነትን ወደ ትግራይ ለመመለስ እየሞከሩ እንደሆነ ጠቅሰው፤ ይህ አካሄድ አደገኛ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተከብሮ በትግራይ ክልል አዲስ ምርጫ መደረግ አለበት ያሉት ሃላፊው፤ ለዚህ ደግሞ የፌዴራል መንግስትና የትግራይ ህዝብ ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የቀድሞ ህወሓት ከጅምሩ የአስተዳደርና የፖለቲካ ችግር ያለበት፣ የትግራይን ሕዝብ የማይመጥንና ጥቅሙን አስከብሮ የማያውቅ ነው ያሉት የመድረኩ ተሳታፊ ሀጎስ አብርሃ (ዶ/ር) ናቸው።   ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ መምህር ገብረኪሮስ ሀይሉ በበኩላቸው፤ የትግራይ ህዝብ የመጀመሪያ ጥያቄ ሰላም እና ልማት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም የትግራይ ህዝብ ልጆቹ ወደ ልማት እንዲሰማሩና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጽኑ ፍላጎት አለው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የፓን አፍሪካኒዝም ሚናዋን የሚያጎሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ነው
Feb 14, 2026 51
አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የፓን አፍሪካኒዝም ሚናዋን የሚያጎሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች መሆኑን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር ፍራንቺስካ ቤሎቤ ገለጹ። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። ኮሚሽነር ፍራንቺስካ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ ጀምሮ በአህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውታለች። የዓድዋ ድል ለአፍሪካ ነጻነት ምልክት መሆኑን ጠቁመው፤ በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ መሪ ሚናዋን ተጫውታለች ብለዋል። በተለይም አፍሪካዊያን አንድ ሆነው የሚገጥማቸውን ፈተና በትብብር እንዲወጡ መሰረት የጣለ እንቅስቃሴ ማድረጓንም ጠቅሰዋል። የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራቾች የህብረቱ መቀመጫ ኢትዮጵያ እንዲሆን መወሰናቸው ኢትዮጵያ ለተጫወተችው ሚና እውቅና የሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል። አፍሪካ እየተለወጠ ባለው ዓለም ድምጿን እና ጥቅሞቿን ለማስከበር በአንድ ላይ መቆም ይገባታል ያሉት ኮሚሽነር ፍራንቺስካ፤ መሰል ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ በጋራ መቆም እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪው መስክ ተሻጋሪ የኢንዱስትሪ ሥርዓት እየገነባች መሆኑን ጠቁመው፤ ለማህበራዊ፣ ኢኮኖሚ ልማት ወሳኝ የሆኑ የውኃ እና ኢነርጂ አቅርቦት ላይ እያከናወነች ያለው ሥራ በምሳሌነት የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል። በተለይም የውኃና የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ሥራዎች ለቀጣናዊ ትስስር ጉልህ ፋይዳ አላቸው ያሉት ኮሚሽነር ፍራንቺስካ፤ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የፓን አፍሪካኒዝም ሚናዋን የሚያጎሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የቀድሞ ሊቀ መንበር ኒኮሳዛና ዲላሚኒ ዙማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በአፍሪካ የሚታሰበውን ትብብርና ብልፅግና እውን ለማድረግ የአህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን ማፋጠን እንደሚገባ ጠቁመዋል። ለዚህ ደግሞ ትብብር እና እንደ አፍሪካ ማሰብ ይገባል ያሉት ዶክተር ኒኮሳዛና፤ የአፍሪካዊያን ኩራት ከሆነው የዓድዋ ድል በህብረት መሥራትን ልንማር ይገባል ብለዋል።
   የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 40
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን።   የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው።   የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል።   የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት።   የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ጥቂት ስለ አዲሱ አፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ 
Feb 14, 2026 74
ጥቂት ስለ አዲሱ አፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። በጉባኤው የአገልግሎት ጊዜያቸውን የጨረሱት የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር እና የአንጎላ ፕሬዝዳንት ጆአኦ ሎሬንዞ ሊቀመንበርነታቸውን ለብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ አስረክበዋል። አዲሱ ሊቀመንበር እና የብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ከእ.አ.አ ጁን 2020 አንስቶ ሀገሪቷን በርዕሰ ብሔርነት እየመሩ ይገኛሉ። ንዳይሺሚዬ ፕሬዝዳንት የሆኑት እ.አ.አ በ2020 ፕሬዝዳንት ፒዬር ንኩሩንዚዛ ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ ነው። የብሩንዲው ፕሬዝዳንት እ.አ.አ ጁን 17 1968 በማዕከላዊ ብሩንዲ ጊቴጋ ግዛት ጊሄታ የተባለ ስፍራ ነው የተወለዱት። 10ኛው የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ የብሩንዲ ብሄራዊ ወታደራዊ ኃይል ምክትል ዋና አዛዥ፣ የፕሬዝዳንት የመከላከያ እና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ እና የሀገር ውስጥ ጉዳይና የህዝብ ደህንነት ሚኒስትር በመሆን ሰርተዋል። በተጨማሪም የፕሬዝዳንት ከፍተኛ አማካሪ እና የብሩንዲ ገዢ ፓርቲ የብሄራዊ የዴሞክራሲ ጥበቃ ምክር ቤት (CNDD-FDD) ዋና ፀሐፊ በመሆንም አገልግለዋል። ፕሬዝዳንት ንዳይሺሚዬ በቀጣናው ዲፕሎማሲ ቀጣናዊ ትስስር መጠናከር ላይ በመሞገት ላይ ጠንካራ ተሟጋች ናቸው። ብሄራዊ መረጋጋት፣ ኢኮኖሚያዊ ልማት እና የፖለቲካ መረጋጋት ማስፈን የመንግስታቸው አበይት አጀንዳዎች ናቸው። የአፍሪካ ህብረት የ2026 ሊቀ መንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ የአፍሪካን የፖሊሲ የትኩረት መስኮች ትግበራን ያስተባብራሉ። ንዳይሺሚዬ በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርነት ለአንድ ዓመት ያገለግላሉ።
የሚታይ
ከሻዕቢያ መንግስት ጋር በማበር የሚመለስ የትግራይ ህዝብ ጥያቄ የለም - የትግራይ ተወላጆች
Feb 14, 2026 65
‎አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡- ከሻዕቢያ መንግስት ጋር በማበር የሚመለስ አንዳች የሰላምና የልማት ጥያቄ የለም ሲሉ የትግራይ ተወላጆች ገለጹ፡፡ ለትግራይ ክልል ብሎም ለኢትዮጵያ ህዝብ ከሻዕቢያ በላይ ጠላት የለም በማለት ነው የገለጹት። የፌዴራል መንግስት በህገ መንግስቱና በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት በትግራይ ክልል ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ ነውም ብለዋል።   የትግራይ ለውጥ ፈላጊዎች ንቅናቄ "ሰላም ለህዝባችን፣ ለውጥ ለወደፊት ተስፋችን” በሚል መሪ ሃሳብ ከክልሉ ተወላጆች ጋር በአዲስ አበባ ምክክር አድርጓል፡፡ የትግራይ የለውጥ ፈላጊዎች ንቅናቄ አባልና የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተደራዳሪ አሰፋ አብርሃ በዚህ ወቅት፤ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ለመፍታት የተፈረመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ ተፈጻሚ አለመሆኑን ጠቅሰዋል። በተለይም ጥቂት የቀድሞ ህወሓት አንጃዎች የኢትዮጵያና የትግራይ ህዝብ ጠላት ከሆነው የሻዕቢያ መንግስት ጋር ተሰልፈው የኢፌዴሪ ህገ መንግስትና የፕሪቶሪያን ስምምነት መጣሳቸውን ተናግረዋል፡፡ ለትግራይ ክልል ብሎም ለኢትዮጵያ ህዝብ ከሻዕቢያ በላይ ጠላት የለም ያሉት አቶ አሰፋ፤ ከሻዕቢያ ኃይል ጋር መሰለፍ ባንዳነት መሆኑን አስረድተዋል። የትግራይ ህዝብ ከሁለተኛ ጥፋት ለመዳን ጦርነትን በመቃወምና በሰላማዊ መንገድ በመታገል ከኋላቀሩ አንጃ መላቀቅ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በትግራይ ክልል ምርጫ ተካሂዶ መደበኛና ህጋዊ መንግስት እንዲኖር መስራት የንቅናቄያቸው ዓላማ መሆኑን በመጥቀስ፤ ከፌዴራል መንግስት ጋር አብሮ መስራት ሀገራዊ ግዴታችን ነው ብለዋል፡፡ የትግራይ የለውጥ ፈላጊዎች ንቅናቄ አባል ሌተናል ጀኔራል ፃድቃን ወልደትንሳኤ፤ የፌዴራል መንግስት ተፈናቃዮችን በመመለስ ከመጀመሪያው ጀምሮ እንቅፋት ሆኖ እንደማያውቅ ገልጸዋል፡፡ የትግራይ የፖለቲካ ችግሮች በሂደት እንዲፈቱና ቅድሚያ ለተፈናቃዮችና ሰብዓዊ ድጋፍ የሚል ስምምነት እንደነበርም አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ የቀድሞ ህወሓት አንጃ የራሱን ፍላጎት ለማሳካት ተፈናቃዮችን እንዳይመለሱ በማድረግ የፖለቲካ መያዣ አድርጓቸዋል ብለዋል፡፡ የፌዴራል መንግስት በህገ መንግስቱና በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት በትግራይ ክልል ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።   የቀድሞው ህወሓት ከሻዕቢያ መንግስትና ሌሎች ፀረ ሰላም ሃይሎች ጋር በመቀናጀት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ጥሶ ለጦርነት እየተዘጋጀ መሆኑንም ሌተናል ጀኔራል ጻድቃን አንስተዋል፡፡ የትግራይ ክልል ችግር የሚፈታው በሰላማዊ መንገድና ከፌዴራል መንግስት ጋር በመተባበር መሆኑንም ጠቅሰዋል። ከሻዕቢያ ጋር በመተባበርና በጦርነት የሚፈታም ሆነ የሚሳካ ጉዳይ እንደሌለ በመግለጽ፤ የትግራይ ህዝብ በየአካባቢው ተደራጅቶ ባንዳና ባዳን መታገል አለበት ብለዋል፡፡   የባይቶና ፓርቲ ሃላፊ ክብሮም በርኸ በበኩላቸው፤ የቀድሞ ህወሓት የትግራይን ህዝብ ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ ስቃዩን ለማብዛት ከሻዕቢያ ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እነዚህ አካላት ከውጭ ጠላት ጋር በማበር ጦርነትን ወደ ትግራይ ለመመለስ እየሞከሩ እንደሆነ ጠቅሰው፤ ይህ አካሄድ አደገኛ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተከብሮ በትግራይ ክልል አዲስ ምርጫ መደረግ አለበት ያሉት ሃላፊው፤ ለዚህ ደግሞ የፌዴራል መንግስትና የትግራይ ህዝብ ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የቀድሞ ህወሓት ከጅምሩ የአስተዳደርና የፖለቲካ ችግር ያለበት፣ የትግራይን ሕዝብ የማይመጥንና ጥቅሙን አስከብሮ የማያውቅ ነው ያሉት የመድረኩ ተሳታፊ ሀጎስ አብርሃ (ዶ/ር) ናቸው።   ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ መምህር ገብረኪሮስ ሀይሉ በበኩላቸው፤ የትግራይ ህዝብ የመጀመሪያ ጥያቄ ሰላም እና ልማት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም የትግራይ ህዝብ ልጆቹ ወደ ልማት እንዲሰማሩና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጽኑ ፍላጎት አለው ብለዋል።
ጥቂት ስለ አዲሱ አፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ 
Feb 14, 2026 74
ጥቂት ስለ አዲሱ አፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። በጉባኤው የአገልግሎት ጊዜያቸውን የጨረሱት የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር እና የአንጎላ ፕሬዝዳንት ጆአኦ ሎሬንዞ ሊቀመንበርነታቸውን ለብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ አስረክበዋል። አዲሱ ሊቀመንበር እና የብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ከእ.አ.አ ጁን 2020 አንስቶ ሀገሪቷን በርዕሰ ብሔርነት እየመሩ ይገኛሉ። ንዳይሺሚዬ ፕሬዝዳንት የሆኑት እ.አ.አ በ2020 ፕሬዝዳንት ፒዬር ንኩሩንዚዛ ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ ነው። የብሩንዲው ፕሬዝዳንት እ.አ.አ ጁን 17 1968 በማዕከላዊ ብሩንዲ ጊቴጋ ግዛት ጊሄታ የተባለ ስፍራ ነው የተወለዱት። 10ኛው የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ የብሩንዲ ብሄራዊ ወታደራዊ ኃይል ምክትል ዋና አዛዥ፣ የፕሬዝዳንት የመከላከያ እና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ እና የሀገር ውስጥ ጉዳይና የህዝብ ደህንነት ሚኒስትር በመሆን ሰርተዋል። በተጨማሪም የፕሬዝዳንት ከፍተኛ አማካሪ እና የብሩንዲ ገዢ ፓርቲ የብሄራዊ የዴሞክራሲ ጥበቃ ምክር ቤት (CNDD-FDD) ዋና ፀሐፊ በመሆንም አገልግለዋል። ፕሬዝዳንት ንዳይሺሚዬ በቀጣናው ዲፕሎማሲ ቀጣናዊ ትስስር መጠናከር ላይ በመሞገት ላይ ጠንካራ ተሟጋች ናቸው። ብሄራዊ መረጋጋት፣ ኢኮኖሚያዊ ልማት እና የፖለቲካ መረጋጋት ማስፈን የመንግስታቸው አበይት አጀንዳዎች ናቸው። የአፍሪካ ህብረት የ2026 ሊቀ መንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ የአፍሪካን የፖሊሲ የትኩረት መስኮች ትግበራን ያስተባብራሉ። ንዳይሺሚዬ በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርነት ለአንድ ዓመት ያገለግላሉ።
የአፍሪካ ሀገራት ለቅርሶች ጥበቃ ልዩ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል - ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ማሪያ ኔቬስ
Feb 14, 2026 42
‎አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ ሀገራት ለቅርሶች ጥበቃ ልዩ ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ የኬፕቨርዴ ፕሬዝዳንት እና የባህል ተፈጥሮ እና ቅርስ ሻምፒዮን ጆሴፍ ማሪያ ኔቬስ ገለጹ። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የኬፕቨርዴ ፕሬዝዳንት እና የባህል ተፈጥሮ እና ቅርስ ሻምፒዮን ጆሴፍ ማሪያ ኔቬስ በቅርስ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ማምሻውን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ‎በአፍሪካ እስካሁን ድረስ ያልታዩ ብዙ ቅርሶች መኖራቸውን ገልጸው፤ እያንዳንዱ የአፍሪካ ሀገር እነዚህን ቅርሶች ወደ ብርሃን ማውጣት እንደሚጠበቅበት አመልክተዋል። ‎የቅርሶችን መመለስ እና የካሳ ሂደት የቅርስ አጀንዳ ማዕከላዊ አካል መሆኑን ጠቁመው፤ ‎በህብረቱ በኩል ለጉዳዩ ትኩረት እንደተሰጠው አውስተዋል። ‎‎ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ በቅርሶች መመለስ ረገድ መሻሻሎች መኖራቸውን ጠቁመው፤ ‎ሆኖም ግን አሁንም የካሳ እና የማካካሻ ፍትሕ እንደሚጎድለው አንስተዋል። ‎እነዚህ ቅርሶች ለልማት ጠቃሚ መሣሪያዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ ከማንነት አንጻርም እጅግ ወሳኝ መሆናቸውን ተናግረው፤ ቅርስ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለልማትም ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ማሪያ ኔቬስ‎ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ቅርሶችን በዩኔስኮ ማስመዝገቡን አስታውሰው፤ ‎ለዚህም ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል። ‎ቅርሶችን የመጠበቅና አዳዲስ ቅርሶችን በመዝገቡ ላይ የመጨመር ሥራዎችን የአፍሪካ ሀገራት በአርአያነት ሊከተሉት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ
Feb 14, 2026 64
‎አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞተሊ ለሶስተኛ ጊዜ የሐገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመመረጣቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ የባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞተሊ ለሶስተኛ ጊዜ የሐገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመመረጣቸው እንኳን ደስ አለዎት እያልኩ የተሰማኝን ደስታ እገልጻለሁ ብለዋል። ‎ ‎የባርቤዶስ ሕዝብ ላደረገው ስኬታማ የዴሞክራሲ ልምምድ አድናቆታቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞትሊ ለባርቤዶስ ሕዝብ እድገት፣ ብልጽግና እና ዘላቂ ልማት ለሚያደርጉት ጥረት መልካም እድል እንዲገጥማቸው ተመኝተዋል። ‎በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጠንካራ ትስስር እና ትብብራችንን ለማጠናከር በጋራ እንሰራለን ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
አፍሪካ እያጋጠሟት ያሉ ተለዋዋጭ ፈተናዎችን በቆራጥነት፣ በፈጠራና በጽናት እየተወጣች ትገኛለች
Feb 14, 2026 90
አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-አፍሪካ እያጋጠሟት ያሉ ተለዋዋጭ ፈተናዎችን በቆራጥነት፣ በፈጠራና በጽናት እየተወጣች እንደምትገኝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ቢያንስ ሁለት ቋሚ የምክር ቤት መቀመጫዎች ሊሰጧት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። የድርጅቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ከ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በተጓዳኝ በአፍሪካና ዓለም አቀፍ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም አፍሪካ በተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ቢያንስ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎች ሊሰጣት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ አህጉሪቱ የዓለም አቀፍ ውሳኔዎች ተቀባይ ብቻ ሳትሆን፣ የወቅቱን የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ቀጥተኛ ውሳኔ ሰጪ መሆን እንዳለባትም ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካ አንጡራ ሀብቶች መበዝበዝ ማቆም እንዳለባቸው የጠቆሙት ዋና ጸሐፊው፤ ምርቶች እሴት ተጨምሮባቸው ለገበያ እንዲቀርቡ ፍትሐዊ የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ ያስፈልጋል ብለዋል።   አሁን ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ለሀብታም ሀገራት ያደላና ለአፍሪካ ኢ-ፍትሐዊ መሆኑን ጠቁመው፣ የአህጉሪቱ የዕዳ ጫና እንዲቃለልና የልማት ባንኮች ብድር እንዲጨምሩ ጠይቀዋል። በሱዳን፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ በሳህልና በምስራቅ አፍሪካ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለመፍታት አፍሪካ መራሽ የሰላም ስራዎች በቋሚ በጀት ሊደገፉ እንደሚገባ አሳስበዋል። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ምክንያት ባልሆነችበት ሁኔታ ከፍተኛውን ዋጋ እየከፈለች መሆኑን በማንሳት፣ የበለጸጉ ሀገራት ለታዳጊ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል፡፡ አፍሪካ እያጋጠሟት ያሉ ተለዋዋጭ ፈተናዎችን በቆራጥነት፣ በፈጠራና በጽናት እየተወጣች ትገኛለችም ብለዋል፡፡ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ ሕብረት መካከል ያለው አጋርነት ከምንጊዜውም በላይ ጠንካራ መሆኑን የገለጹት ዋና ጸሐፊው፣ በቀጣይም በሰላም፣ በዘላቂ ልማትና በሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ላይ ያለው ስትራቴጂካዊ ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ጥቂት ስለ አዲሱ አፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ 
Feb 14, 2026 74
ጥቂት ስለ አዲሱ አፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። በጉባኤው የአገልግሎት ጊዜያቸውን የጨረሱት የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር እና የአንጎላ ፕሬዝዳንት ጆአኦ ሎሬንዞ ሊቀመንበርነታቸውን ለብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ አስረክበዋል። አዲሱ ሊቀመንበር እና የብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ከእ.አ.አ ጁን 2020 አንስቶ ሀገሪቷን በርዕሰ ብሔርነት እየመሩ ይገኛሉ። ንዳይሺሚዬ ፕሬዝዳንት የሆኑት እ.አ.አ በ2020 ፕሬዝዳንት ፒዬር ንኩሩንዚዛ ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ ነው። የብሩንዲው ፕሬዝዳንት እ.አ.አ ጁን 17 1968 በማዕከላዊ ብሩንዲ ጊቴጋ ግዛት ጊሄታ የተባለ ስፍራ ነው የተወለዱት። 10ኛው የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ የብሩንዲ ብሄራዊ ወታደራዊ ኃይል ምክትል ዋና አዛዥ፣ የፕሬዝዳንት የመከላከያ እና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ እና የሀገር ውስጥ ጉዳይና የህዝብ ደህንነት ሚኒስትር በመሆን ሰርተዋል። በተጨማሪም የፕሬዝዳንት ከፍተኛ አማካሪ እና የብሩንዲ ገዢ ፓርቲ የብሄራዊ የዴሞክራሲ ጥበቃ ምክር ቤት (CNDD-FDD) ዋና ፀሐፊ በመሆንም አገልግለዋል። ፕሬዝዳንት ንዳይሺሚዬ በቀጣናው ዲፕሎማሲ ቀጣናዊ ትስስር መጠናከር ላይ በመሞገት ላይ ጠንካራ ተሟጋች ናቸው። ብሄራዊ መረጋጋት፣ ኢኮኖሚያዊ ልማት እና የፖለቲካ መረጋጋት ማስፈን የመንግስታቸው አበይት አጀንዳዎች ናቸው። የአፍሪካ ህብረት የ2026 ሊቀ መንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ የአፍሪካን የፖሊሲ የትኩረት መስኮች ትግበራን ያስተባብራሉ። ንዳይሺሚዬ በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርነት ለአንድ ዓመት ያገለግላሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ
Feb 14, 2026 64
‎አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞተሊ ለሶስተኛ ጊዜ የሐገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመመረጣቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ የባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞተሊ ለሶስተኛ ጊዜ የሐገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመመረጣቸው እንኳን ደስ አለዎት እያልኩ የተሰማኝን ደስታ እገልጻለሁ ብለዋል። ‎ ‎የባርቤዶስ ሕዝብ ላደረገው ስኬታማ የዴሞክራሲ ልምምድ አድናቆታቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞትሊ ለባርቤዶስ ሕዝብ እድገት፣ ብልጽግና እና ዘላቂ ልማት ለሚያደርጉት ጥረት መልካም እድል እንዲገጥማቸው ተመኝተዋል። ‎በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጠንካራ ትስስር እና ትብብራችንን ለማጠናከር በጋራ እንሰራለን ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ በተሰማራባቸው አካባቢዎች ሁሉ ተልእኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየፈፀመ ነው 
Feb 14, 2026 107
ጋምቤላ ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-በሀገር መከላከያ ሰራዊት የዳሎል ማእከላዊ እዝ በተሰማራባቸው አካባቢዎች ሁሉ ግዳጅና ተልእኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየፈፀመ መሆኑን የእዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ ገለጹ። የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ በተለይም በምእራብ የሀገሪቷ ክፍሎችና በደቡብ ሱዳን ድንበር አካባቢዎች የሀገርንና የዜጎችን ሰላም በማስጠበቅ ረገድ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን በተመለከተ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በኢትዮጵያና በደቡብ ሱዳን ድንበር አካባቢዎች ሰላምና ጸጥታን ለማወክ ሙከራዎች እንደነበሩ አስታውሰዋል። በአካባቢው የተሰማራው የዳሎል ማእከላዊ እዝ ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን በጥፋት እንቅስቃሴ ላይ በነበሩ አካላት ላይ ጠንካራ እርምጃ መውሰዱን አንስተዋል። በተለይም በሁለቱ አገራት ድንበር አካባቢ አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን የሁለቱ ሀገራት የጸጥታ አካላት በጋራ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ተችሏል ብለዋል። በጋምቤላም ይሁን በደቡብ ሱዳን ድንበር አካባቢዎች አሁን ላይ አስተማማኝ ሰላም ማስፈን መቻሉን ተናግረዋል። የዳሎል ማእከላዊ እዝ በተሰማራባቸው አካባቢዎች ሁሉ ተልእኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየፈፀመ መሆኑን የገለጹት ሌተናል ጀነራሉ በቀጣይም አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
አፍሪካ እያጋጠሟት ያሉ ተለዋዋጭ ፈተናዎችን በቆራጥነት፣ በፈጠራና በጽናት እየተወጣች ትገኛለች
Feb 14, 2026 90
አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-አፍሪካ እያጋጠሟት ያሉ ተለዋዋጭ ፈተናዎችን በቆራጥነት፣ በፈጠራና በጽናት እየተወጣች እንደምትገኝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ቢያንስ ሁለት ቋሚ የምክር ቤት መቀመጫዎች ሊሰጧት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። የድርጅቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ከ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በተጓዳኝ በአፍሪካና ዓለም አቀፍ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም አፍሪካ በተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ቢያንስ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎች ሊሰጣት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ አህጉሪቱ የዓለም አቀፍ ውሳኔዎች ተቀባይ ብቻ ሳትሆን፣ የወቅቱን የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ቀጥተኛ ውሳኔ ሰጪ መሆን እንዳለባትም ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካ አንጡራ ሀብቶች መበዝበዝ ማቆም እንዳለባቸው የጠቆሙት ዋና ጸሐፊው፤ ምርቶች እሴት ተጨምሮባቸው ለገበያ እንዲቀርቡ ፍትሐዊ የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ ያስፈልጋል ብለዋል።   አሁን ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ለሀብታም ሀገራት ያደላና ለአፍሪካ ኢ-ፍትሐዊ መሆኑን ጠቁመው፣ የአህጉሪቱ የዕዳ ጫና እንዲቃለልና የልማት ባንኮች ብድር እንዲጨምሩ ጠይቀዋል። በሱዳን፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ በሳህልና በምስራቅ አፍሪካ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለመፍታት አፍሪካ መራሽ የሰላም ስራዎች በቋሚ በጀት ሊደገፉ እንደሚገባ አሳስበዋል። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ምክንያት ባልሆነችበት ሁኔታ ከፍተኛውን ዋጋ እየከፈለች መሆኑን በማንሳት፣ የበለጸጉ ሀገራት ለታዳጊ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል፡፡ አፍሪካ እያጋጠሟት ያሉ ተለዋዋጭ ፈተናዎችን በቆራጥነት፣ በፈጠራና በጽናት እየተወጣች ትገኛለችም ብለዋል፡፡ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ ሕብረት መካከል ያለው አጋርነት ከምንጊዜውም በላይ ጠንካራ መሆኑን የገለጹት ዋና ጸሐፊው፣ በቀጣይም በሰላም፣ በዘላቂ ልማትና በሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ላይ ያለው ስትራቴጂካዊ ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር በላቀ ብቃት የሚጠብቁ ጀግኖች እያፈራ ነው 
Feb 14, 2026 81
ሀዋሳ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር በላቀ ብቃት የሚጠብቁ ጀግኖች እያፈራ ነው ሲሉ የዕዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ገለጹ። የልዩ ዘመቻዎቸ ዕዝ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን በማስመልከት በሀዋሳ የ10 ኪሎሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ተካሂዷል።   የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፣ ሰራዊቱ የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ለማስጠበቅ የትኛውንም መስዋዕትነት በመክፈል አኩሪ ገድል እያስመዘገበ ነው። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በ65 ዓመታት ጉዞው ሀገርን ከፍ የሚያደርጉና ዳር ድንበሯን የሚጠብቁ ጀግኖች አፍርቷል ነው ያሉት። እነዚህ ጀግኖች የሕይወት መስዋዕትነት ጭምር በመክፈል ሀገርና ህዝብ የማይረሳው ታሪክ መጻፍ የቻሉ መሆናቸውን በማንሳት። የዕዙ የምስረታ በዓል መከበር እነዚህ ጀግኖች እንዲታወሱና ትውልዱ ከሰራዊቱ የሀገር ፍቅር፣ ክብርና መስዋዕትነትን እንዲማር የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ሀገርንና ህዝብን ሁሌም በዝግጁነት የሚጠብቅ፣ የውጊያ ማርሽ ቀያሪና የመሬት ላይ ድሮን ነው ብለዋል። አትሌቶችን ጨምሮ ሁሉም ዜጋ የሚያጋጥመውን መሰናክል በአሸናፊነት በመወጣት ለሀገሩ ከፍታ ሊተጋ እንደሚገባ አሳስበዋል።   የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው፣ የሲዳማ ህዝብና የልዩ ዘመቻዎቸ ዕዝ ለ65 ዓመታት ጠንካራ ቁርኝትና አንድነት እንዳላቸው አንስተዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የትኛውንም የጠላት ሃይል በብቃት መመከት የሚችል ጠንካራ አቅም መገንባቱንም ተናግረዋል። ዕዙ ለትውልዱ ኩራት፡ የሀገር ክብር ምልክት መሆኑንም አመልክተዋል። በሩጫ ውድድሩ በወንዶች የግል ተወዳዳሪው አትሌት ቢንያም መላክ በሴቶች ደግሞ ውድነሽ አለሙ የአንደኝነት ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል። በሁለቱም ጾታዎች ከአንደኛ እስከ አምስተኛ የወጡ አትሌቶች ከዕለቱ የክብር እንግዶች የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ኢትዮጵያ ታላላቅ ኹነቶችን ለማስተናገድ የፈጠረችው አቅምና ውጤታማነት እየታየ ነው
Feb 14, 2026 80
አዲስ አበባ፤የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ታላላቅ ዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ኹነቶችን ለማስተናገድ የፈጠረችው አቅምና ውጤታማነት በተግባር እየታየ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ የጉባዔው መክፈቻ መርሃ ግብር እንደተጠናቀቀ በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ትናንት ሁለተኛውን የጣሊያን-አፍሪካ ስብሰባ በስኬት በማስተናገድ ዛሬ ደግሞ 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔን በስኬት እያስተናገደች ትገኛለች ብለዋል። በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ሁለተኛው የጣሊያን አፍሪካ ጉባዔ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸው፤ ጉባዔው በአዲስ አበባ መካሄዱ የመዲናዋን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ጉባዔው በአፍሪካና ጣሊያን መካከል ያሉ ግንኙነቶችን ስትራቴጂክ በሆነ መንገድ ወደ አጋርነት ማሳደግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች የተቀመጡበት መሆኑንም ተናግረዋል። በጉባዔው ስድስት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ውይይት መደረጉን ጠቅሰው፤ ከእነዚህም መካከል የጤና ጉዳይ አንዱና ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እየሰራች ያለችውን ተግባር ማጠናከር የሚያስችል ነው ብለዋል። በትምህርትና ስልጠናም ኢትዮጵያ ትምህርት ለትውልድ በሚል ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ በትኩረት እየሰራችበት ያለ ዘርፍ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከተለያዩ አማራጮች ንጹህ ኢነርጂ ለማመንጨት እየሰራች መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ የጣሊያን ትብብር ታዳሽ ኃይል ለማምረት የሚደረገውን ጥረት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተናግረዋል። ግብርናና ውሃም ውይይት የተደረገባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በመሪ ሀሳብ መሰረት ውሃ ለልማትና እድገት አቅጣጫዎች ወሳኝ መሆኑን አመልክተው፤ ኢትዮጵያ ያላትን የውሃ ሀብት በውጤታማነትና በመርህ ላይ ተመስርታ ለመጠቀም ያላትን ዝግጁነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባዔው ላይ ኢትዮጵያ ፍትሃዊ የውሃ ተጠቃሚነትና የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረትና እያከናወነች ያለውን የልማት ስራዎች መግለፃቸውን አንስተዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራትን ለማስተዋወቅ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ከበርካታ ባለድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን መደረጋቸውን አንስተው፤ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የምታጠናክርበት መሆኑን ገልፀዋል። በርካታ መሪዎች ጉባዔውን ለመታደም ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውን ጠቅሰው፤ ይህም ኢትዮጵያ ትላልቅ ኹነቶችን ለማስተናገድ የፈጠረችውን አቅምና ውጤታማነቷን ማሳያ ነው ብለዋል።
የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል-የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት 
Feb 14, 2026 117
አዲስ አበባ፤የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። እየተካሄደ የሚገኘውን 39ኛውን የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ አስመልክቶ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ መግለጫ ሰጥተዋል። ሚኒስትር ዴኤታው በዚህ ወቅት፥ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ኢትዮጵያ በርካታ ኮንፈረንሶችን የማስተናገድ አቅም ዳግም ያረጋገጠችበት መሆኑን ገልጸዋል።   ጉባኤው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል መሆኗን ከማረጋገጥ ባለፈ የሀገሪቱን ገጽታ በማጉላት በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። ጉባኤው ለኢትዮጵያ የቱሪዝም ገቢን በማሳደግ ረገድም ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። በጉባኤው የበርካታ ሀገራት መሪዎች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸው፥ በጣም ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል። 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ” ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በህብረቱ መቀመጫ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
ፖለቲካ
ጥቂት ስለ አዲሱ አፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ 
Feb 14, 2026 74
ጥቂት ስለ አዲሱ አፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። በጉባኤው የአገልግሎት ጊዜያቸውን የጨረሱት የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር እና የአንጎላ ፕሬዝዳንት ጆአኦ ሎሬንዞ ሊቀመንበርነታቸውን ለብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ አስረክበዋል። አዲሱ ሊቀመንበር እና የብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ከእ.አ.አ ጁን 2020 አንስቶ ሀገሪቷን በርዕሰ ብሔርነት እየመሩ ይገኛሉ። ንዳይሺሚዬ ፕሬዝዳንት የሆኑት እ.አ.አ በ2020 ፕሬዝዳንት ፒዬር ንኩሩንዚዛ ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ ነው። የብሩንዲው ፕሬዝዳንት እ.አ.አ ጁን 17 1968 በማዕከላዊ ብሩንዲ ጊቴጋ ግዛት ጊሄታ የተባለ ስፍራ ነው የተወለዱት። 10ኛው የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ የብሩንዲ ብሄራዊ ወታደራዊ ኃይል ምክትል ዋና አዛዥ፣ የፕሬዝዳንት የመከላከያ እና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ እና የሀገር ውስጥ ጉዳይና የህዝብ ደህንነት ሚኒስትር በመሆን ሰርተዋል። በተጨማሪም የፕሬዝዳንት ከፍተኛ አማካሪ እና የብሩንዲ ገዢ ፓርቲ የብሄራዊ የዴሞክራሲ ጥበቃ ምክር ቤት (CNDD-FDD) ዋና ፀሐፊ በመሆንም አገልግለዋል። ፕሬዝዳንት ንዳይሺሚዬ በቀጣናው ዲፕሎማሲ ቀጣናዊ ትስስር መጠናከር ላይ በመሞገት ላይ ጠንካራ ተሟጋች ናቸው። ብሄራዊ መረጋጋት፣ ኢኮኖሚያዊ ልማት እና የፖለቲካ መረጋጋት ማስፈን የመንግስታቸው አበይት አጀንዳዎች ናቸው። የአፍሪካ ህብረት የ2026 ሊቀ መንበር ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ የአፍሪካን የፖሊሲ የትኩረት መስኮች ትግበራን ያስተባብራሉ። ንዳይሺሚዬ በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርነት ለአንድ ዓመት ያገለግላሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ
Feb 14, 2026 64
‎አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞተሊ ለሶስተኛ ጊዜ የሐገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመመረጣቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ የባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞተሊ ለሶስተኛ ጊዜ የሐገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመመረጣቸው እንኳን ደስ አለዎት እያልኩ የተሰማኝን ደስታ እገልጻለሁ ብለዋል። ‎ ‎የባርቤዶስ ሕዝብ ላደረገው ስኬታማ የዴሞክራሲ ልምምድ አድናቆታቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞትሊ ለባርቤዶስ ሕዝብ እድገት፣ ብልጽግና እና ዘላቂ ልማት ለሚያደርጉት ጥረት መልካም እድል እንዲገጥማቸው ተመኝተዋል። ‎በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጠንካራ ትስስር እና ትብብራችንን ለማጠናከር በጋራ እንሰራለን ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ በተሰማራባቸው አካባቢዎች ሁሉ ተልእኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየፈፀመ ነው 
Feb 14, 2026 107
ጋምቤላ ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-በሀገር መከላከያ ሰራዊት የዳሎል ማእከላዊ እዝ በተሰማራባቸው አካባቢዎች ሁሉ ግዳጅና ተልእኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየፈፀመ መሆኑን የእዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ ገለጹ። የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ በተለይም በምእራብ የሀገሪቷ ክፍሎችና በደቡብ ሱዳን ድንበር አካባቢዎች የሀገርንና የዜጎችን ሰላም በማስጠበቅ ረገድ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን በተመለከተ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በኢትዮጵያና በደቡብ ሱዳን ድንበር አካባቢዎች ሰላምና ጸጥታን ለማወክ ሙከራዎች እንደነበሩ አስታውሰዋል። በአካባቢው የተሰማራው የዳሎል ማእከላዊ እዝ ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን በጥፋት እንቅስቃሴ ላይ በነበሩ አካላት ላይ ጠንካራ እርምጃ መውሰዱን አንስተዋል። በተለይም በሁለቱ አገራት ድንበር አካባቢ አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን የሁለቱ ሀገራት የጸጥታ አካላት በጋራ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ተችሏል ብለዋል። በጋምቤላም ይሁን በደቡብ ሱዳን ድንበር አካባቢዎች አሁን ላይ አስተማማኝ ሰላም ማስፈን መቻሉን ተናግረዋል። የዳሎል ማእከላዊ እዝ በተሰማራባቸው አካባቢዎች ሁሉ ተልእኮውን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየፈፀመ መሆኑን የገለጹት ሌተናል ጀነራሉ በቀጣይም አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
አፍሪካ እያጋጠሟት ያሉ ተለዋዋጭ ፈተናዎችን በቆራጥነት፣ በፈጠራና በጽናት እየተወጣች ትገኛለች
Feb 14, 2026 90
አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-አፍሪካ እያጋጠሟት ያሉ ተለዋዋጭ ፈተናዎችን በቆራጥነት፣ በፈጠራና በጽናት እየተወጣች እንደምትገኝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ቢያንስ ሁለት ቋሚ የምክር ቤት መቀመጫዎች ሊሰጧት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። የድርጅቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ከ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በተጓዳኝ በአፍሪካና ዓለም አቀፍ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም አፍሪካ በተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ቢያንስ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎች ሊሰጣት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ አህጉሪቱ የዓለም አቀፍ ውሳኔዎች ተቀባይ ብቻ ሳትሆን፣ የወቅቱን የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ቀጥተኛ ውሳኔ ሰጪ መሆን እንዳለባትም ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካ አንጡራ ሀብቶች መበዝበዝ ማቆም እንዳለባቸው የጠቆሙት ዋና ጸሐፊው፤ ምርቶች እሴት ተጨምሮባቸው ለገበያ እንዲቀርቡ ፍትሐዊ የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ ያስፈልጋል ብለዋል።   አሁን ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ለሀብታም ሀገራት ያደላና ለአፍሪካ ኢ-ፍትሐዊ መሆኑን ጠቁመው፣ የአህጉሪቱ የዕዳ ጫና እንዲቃለልና የልማት ባንኮች ብድር እንዲጨምሩ ጠይቀዋል። በሱዳን፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ በሳህልና በምስራቅ አፍሪካ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለመፍታት አፍሪካ መራሽ የሰላም ስራዎች በቋሚ በጀት ሊደገፉ እንደሚገባ አሳስበዋል። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ምክንያት ባልሆነችበት ሁኔታ ከፍተኛውን ዋጋ እየከፈለች መሆኑን በማንሳት፣ የበለጸጉ ሀገራት ለታዳጊ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል፡፡ አፍሪካ እያጋጠሟት ያሉ ተለዋዋጭ ፈተናዎችን በቆራጥነት፣ በፈጠራና በጽናት እየተወጣች ትገኛለችም ብለዋል፡፡ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ ሕብረት መካከል ያለው አጋርነት ከምንጊዜውም በላይ ጠንካራ መሆኑን የገለጹት ዋና ጸሐፊው፣ በቀጣይም በሰላም፣ በዘላቂ ልማትና በሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ላይ ያለው ስትራቴጂካዊ ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር በላቀ ብቃት የሚጠብቁ ጀግኖች እያፈራ ነው 
Feb 14, 2026 81
ሀዋሳ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር በላቀ ብቃት የሚጠብቁ ጀግኖች እያፈራ ነው ሲሉ የዕዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ገለጹ። የልዩ ዘመቻዎቸ ዕዝ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን በማስመልከት በሀዋሳ የ10 ኪሎሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ተካሂዷል።   የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፣ ሰራዊቱ የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ለማስጠበቅ የትኛውንም መስዋዕትነት በመክፈል አኩሪ ገድል እያስመዘገበ ነው። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በ65 ዓመታት ጉዞው ሀገርን ከፍ የሚያደርጉና ዳር ድንበሯን የሚጠብቁ ጀግኖች አፍርቷል ነው ያሉት። እነዚህ ጀግኖች የሕይወት መስዋዕትነት ጭምር በመክፈል ሀገርና ህዝብ የማይረሳው ታሪክ መጻፍ የቻሉ መሆናቸውን በማንሳት። የዕዙ የምስረታ በዓል መከበር እነዚህ ጀግኖች እንዲታወሱና ትውልዱ ከሰራዊቱ የሀገር ፍቅር፣ ክብርና መስዋዕትነትን እንዲማር የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ሀገርንና ህዝብን ሁሌም በዝግጁነት የሚጠብቅ፣ የውጊያ ማርሽ ቀያሪና የመሬት ላይ ድሮን ነው ብለዋል። አትሌቶችን ጨምሮ ሁሉም ዜጋ የሚያጋጥመውን መሰናክል በአሸናፊነት በመወጣት ለሀገሩ ከፍታ ሊተጋ እንደሚገባ አሳስበዋል።   የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው፣ የሲዳማ ህዝብና የልዩ ዘመቻዎቸ ዕዝ ለ65 ዓመታት ጠንካራ ቁርኝትና አንድነት እንዳላቸው አንስተዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የትኛውንም የጠላት ሃይል በብቃት መመከት የሚችል ጠንካራ አቅም መገንባቱንም ተናግረዋል። ዕዙ ለትውልዱ ኩራት፡ የሀገር ክብር ምልክት መሆኑንም አመልክተዋል። በሩጫ ውድድሩ በወንዶች የግል ተወዳዳሪው አትሌት ቢንያም መላክ በሴቶች ደግሞ ውድነሽ አለሙ የአንደኝነት ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል። በሁለቱም ጾታዎች ከአንደኛ እስከ አምስተኛ የወጡ አትሌቶች ከዕለቱ የክብር እንግዶች የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ኢትዮጵያ ታላላቅ ኹነቶችን ለማስተናገድ የፈጠረችው አቅምና ውጤታማነት እየታየ ነው
Feb 14, 2026 80
አዲስ አበባ፤የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ታላላቅ ዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ኹነቶችን ለማስተናገድ የፈጠረችው አቅምና ውጤታማነት በተግባር እየታየ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ የጉባዔው መክፈቻ መርሃ ግብር እንደተጠናቀቀ በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ትናንት ሁለተኛውን የጣሊያን-አፍሪካ ስብሰባ በስኬት በማስተናገድ ዛሬ ደግሞ 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔን በስኬት እያስተናገደች ትገኛለች ብለዋል። በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ሁለተኛው የጣሊያን አፍሪካ ጉባዔ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸው፤ ጉባዔው በአዲስ አበባ መካሄዱ የመዲናዋን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ጉባዔው በአፍሪካና ጣሊያን መካከል ያሉ ግንኙነቶችን ስትራቴጂክ በሆነ መንገድ ወደ አጋርነት ማሳደግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች የተቀመጡበት መሆኑንም ተናግረዋል። በጉባዔው ስድስት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ውይይት መደረጉን ጠቅሰው፤ ከእነዚህም መካከል የጤና ጉዳይ አንዱና ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እየሰራች ያለችውን ተግባር ማጠናከር የሚያስችል ነው ብለዋል። በትምህርትና ስልጠናም ኢትዮጵያ ትምህርት ለትውልድ በሚል ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ በትኩረት እየሰራችበት ያለ ዘርፍ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከተለያዩ አማራጮች ንጹህ ኢነርጂ ለማመንጨት እየሰራች መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ የጣሊያን ትብብር ታዳሽ ኃይል ለማምረት የሚደረገውን ጥረት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተናግረዋል። ግብርናና ውሃም ውይይት የተደረገባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በመሪ ሀሳብ መሰረት ውሃ ለልማትና እድገት አቅጣጫዎች ወሳኝ መሆኑን አመልክተው፤ ኢትዮጵያ ያላትን የውሃ ሀብት በውጤታማነትና በመርህ ላይ ተመስርታ ለመጠቀም ያላትን ዝግጁነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባዔው ላይ ኢትዮጵያ ፍትሃዊ የውሃ ተጠቃሚነትና የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረትና እያከናወነች ያለውን የልማት ስራዎች መግለፃቸውን አንስተዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራትን ለማስተዋወቅ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ከበርካታ ባለድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን መደረጋቸውን አንስተው፤ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የምታጠናክርበት መሆኑን ገልፀዋል። በርካታ መሪዎች ጉባዔውን ለመታደም ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውን ጠቅሰው፤ ይህም ኢትዮጵያ ትላልቅ ኹነቶችን ለማስተናገድ የፈጠረችውን አቅምና ውጤታማነቷን ማሳያ ነው ብለዋል።
የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል-የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት 
Feb 14, 2026 117
አዲስ አበባ፤የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። እየተካሄደ የሚገኘውን 39ኛውን የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ አስመልክቶ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ መግለጫ ሰጥተዋል። ሚኒስትር ዴኤታው በዚህ ወቅት፥ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ኢትዮጵያ በርካታ ኮንፈረንሶችን የማስተናገድ አቅም ዳግም ያረጋገጠችበት መሆኑን ገልጸዋል።   ጉባኤው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል መሆኗን ከማረጋገጥ ባለፈ የሀገሪቱን ገጽታ በማጉላት በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። ጉባኤው ለኢትዮጵያ የቱሪዝም ገቢን በማሳደግ ረገድም ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። በጉባኤው የበርካታ ሀገራት መሪዎች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸው፥ በጣም ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል። 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ” ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በህብረቱ መቀመጫ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበራዊ
ከሻዕቢያ መንግስት ጋር በማበር የሚመለስ የትግራይ ህዝብ ጥያቄ የለም - የትግራይ ተወላጆች
Feb 14, 2026 65
‎አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡- ከሻዕቢያ መንግስት ጋር በማበር የሚመለስ አንዳች የሰላምና የልማት ጥያቄ የለም ሲሉ የትግራይ ተወላጆች ገለጹ፡፡ ለትግራይ ክልል ብሎም ለኢትዮጵያ ህዝብ ከሻዕቢያ በላይ ጠላት የለም በማለት ነው የገለጹት። የፌዴራል መንግስት በህገ መንግስቱና በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት በትግራይ ክልል ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ ነውም ብለዋል።   የትግራይ ለውጥ ፈላጊዎች ንቅናቄ "ሰላም ለህዝባችን፣ ለውጥ ለወደፊት ተስፋችን” በሚል መሪ ሃሳብ ከክልሉ ተወላጆች ጋር በአዲስ አበባ ምክክር አድርጓል፡፡ የትግራይ የለውጥ ፈላጊዎች ንቅናቄ አባልና የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተደራዳሪ አሰፋ አብርሃ በዚህ ወቅት፤ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ለመፍታት የተፈረመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ ተፈጻሚ አለመሆኑን ጠቅሰዋል። በተለይም ጥቂት የቀድሞ ህወሓት አንጃዎች የኢትዮጵያና የትግራይ ህዝብ ጠላት ከሆነው የሻዕቢያ መንግስት ጋር ተሰልፈው የኢፌዴሪ ህገ መንግስትና የፕሪቶሪያን ስምምነት መጣሳቸውን ተናግረዋል፡፡ ለትግራይ ክልል ብሎም ለኢትዮጵያ ህዝብ ከሻዕቢያ በላይ ጠላት የለም ያሉት አቶ አሰፋ፤ ከሻዕቢያ ኃይል ጋር መሰለፍ ባንዳነት መሆኑን አስረድተዋል። የትግራይ ህዝብ ከሁለተኛ ጥፋት ለመዳን ጦርነትን በመቃወምና በሰላማዊ መንገድ በመታገል ከኋላቀሩ አንጃ መላቀቅ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በትግራይ ክልል ምርጫ ተካሂዶ መደበኛና ህጋዊ መንግስት እንዲኖር መስራት የንቅናቄያቸው ዓላማ መሆኑን በመጥቀስ፤ ከፌዴራል መንግስት ጋር አብሮ መስራት ሀገራዊ ግዴታችን ነው ብለዋል፡፡ የትግራይ የለውጥ ፈላጊዎች ንቅናቄ አባል ሌተናል ጀኔራል ፃድቃን ወልደትንሳኤ፤ የፌዴራል መንግስት ተፈናቃዮችን በመመለስ ከመጀመሪያው ጀምሮ እንቅፋት ሆኖ እንደማያውቅ ገልጸዋል፡፡ የትግራይ የፖለቲካ ችግሮች በሂደት እንዲፈቱና ቅድሚያ ለተፈናቃዮችና ሰብዓዊ ድጋፍ የሚል ስምምነት እንደነበርም አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ የቀድሞ ህወሓት አንጃ የራሱን ፍላጎት ለማሳካት ተፈናቃዮችን እንዳይመለሱ በማድረግ የፖለቲካ መያዣ አድርጓቸዋል ብለዋል፡፡ የፌዴራል መንግስት በህገ መንግስቱና በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት በትግራይ ክልል ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።   የቀድሞው ህወሓት ከሻዕቢያ መንግስትና ሌሎች ፀረ ሰላም ሃይሎች ጋር በመቀናጀት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ጥሶ ለጦርነት እየተዘጋጀ መሆኑንም ሌተናል ጀኔራል ጻድቃን አንስተዋል፡፡ የትግራይ ክልል ችግር የሚፈታው በሰላማዊ መንገድና ከፌዴራል መንግስት ጋር በመተባበር መሆኑንም ጠቅሰዋል። ከሻዕቢያ ጋር በመተባበርና በጦርነት የሚፈታም ሆነ የሚሳካ ጉዳይ እንደሌለ በመግለጽ፤ የትግራይ ህዝብ በየአካባቢው ተደራጅቶ ባንዳና ባዳን መታገል አለበት ብለዋል፡፡   የባይቶና ፓርቲ ሃላፊ ክብሮም በርኸ በበኩላቸው፤ የቀድሞ ህወሓት የትግራይን ህዝብ ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ ስቃዩን ለማብዛት ከሻዕቢያ ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እነዚህ አካላት ከውጭ ጠላት ጋር በማበር ጦርነትን ወደ ትግራይ ለመመለስ እየሞከሩ እንደሆነ ጠቅሰው፤ ይህ አካሄድ አደገኛ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተከብሮ በትግራይ ክልል አዲስ ምርጫ መደረግ አለበት ያሉት ሃላፊው፤ ለዚህ ደግሞ የፌዴራል መንግስትና የትግራይ ህዝብ ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የቀድሞ ህወሓት ከጅምሩ የአስተዳደርና የፖለቲካ ችግር ያለበት፣ የትግራይን ሕዝብ የማይመጥንና ጥቅሙን አስከብሮ የማያውቅ ነው ያሉት የመድረኩ ተሳታፊ ሀጎስ አብርሃ (ዶ/ር) ናቸው።   ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ መምህር ገብረኪሮስ ሀይሉ በበኩላቸው፤ የትግራይ ህዝብ የመጀመሪያ ጥያቄ ሰላም እና ልማት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም የትግራይ ህዝብ ልጆቹ ወደ ልማት እንዲሰማሩና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጽኑ ፍላጎት አለው ብለዋል።
የአፍሪካ ሀገራት ለቅርሶች ጥበቃ ልዩ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል - ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ማሪያ ኔቬስ
Feb 14, 2026 42
‎አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ ሀገራት ለቅርሶች ጥበቃ ልዩ ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ የኬፕቨርዴ ፕሬዝዳንት እና የባህል ተፈጥሮ እና ቅርስ ሻምፒዮን ጆሴፍ ማሪያ ኔቬስ ገለጹ። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የኬፕቨርዴ ፕሬዝዳንት እና የባህል ተፈጥሮ እና ቅርስ ሻምፒዮን ጆሴፍ ማሪያ ኔቬስ በቅርስ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ማምሻውን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ‎በአፍሪካ እስካሁን ድረስ ያልታዩ ብዙ ቅርሶች መኖራቸውን ገልጸው፤ እያንዳንዱ የአፍሪካ ሀገር እነዚህን ቅርሶች ወደ ብርሃን ማውጣት እንደሚጠበቅበት አመልክተዋል። ‎የቅርሶችን መመለስ እና የካሳ ሂደት የቅርስ አጀንዳ ማዕከላዊ አካል መሆኑን ጠቁመው፤ ‎በህብረቱ በኩል ለጉዳዩ ትኩረት እንደተሰጠው አውስተዋል። ‎‎ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ በቅርሶች መመለስ ረገድ መሻሻሎች መኖራቸውን ጠቁመው፤ ‎ሆኖም ግን አሁንም የካሳ እና የማካካሻ ፍትሕ እንደሚጎድለው አንስተዋል። ‎እነዚህ ቅርሶች ለልማት ጠቃሚ መሣሪያዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ ከማንነት አንጻርም እጅግ ወሳኝ መሆናቸውን ተናግረው፤ ቅርስ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለልማትም ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ማሪያ ኔቬስ‎ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ቅርሶችን በዩኔስኮ ማስመዝገቡን አስታውሰው፤ ‎ለዚህም ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል። ‎ቅርሶችን የመጠበቅና አዳዲስ ቅርሶችን በመዝገቡ ላይ የመጨመር ሥራዎችን የአፍሪካ ሀገራት በአርአያነት ሊከተሉት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአፍሪካ መድኃኒት ኤጀንሲ የተጣለበትን አህጉራዊ ተልዕኮ በብቃት እንዲወጣ የአባል አገራት የፋይናንስ አስተዋጽኦ ሊጠናከር ይገባል
Feb 14, 2026 84
አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ መድኃኒት ኤጀንሲ (AMA) የተጣለበትን አህጉራዊ ተልዕኮ በብቃት እንዲወጣ የአባል አገራት የፋይናንስ አስተዋጽኦ ሊጠናከር እንደሚገባ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ደለሰ ሚሚ ዳርኮ ገለጹ። ኤጀንሲው "ለከፍተኛ ጥራት የሕክምና ምርቶች እና ለአፍሪካ የጤና ደህንነት የአፍሪካ መድኃኒት ኤጀንሲ ስምምነትን ማፋጠን" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ የውይይት መድረክ አካሂዷል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ደለሰ ሚሚ ዳርኮ በዚሁ ወቅት፤ ኤጀንሲው የአፍሪካ ዜጎች ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ጥራቱን የጠበቀና ውጤታማ የሕክምና ምርቶችን በወቅቱ እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም የመድኃኒት ቁጥጥር ደንቦችን በአህጉር ደረጃ ማቀናጀትና የቁጥጥር የመረጃ ቋቶችን እንደሚገነባ ጠቅሰው በአህጉሪቱ የመድኃኒት ማምረቻዎችን ማቋቋም እንዲሁም በዘርፉ የሚታዩ የፈጠራ ስራዎችን ያበረታታል ብለዋል፡፡   ኤጀንሲው ወደ ሙሉ ሥራ እንዳይገባ የሕጋዊ ስምምነት መዘግየት እና የፋይናንስ እጥረት እንቅፋት እንደሆኑበት ጠቁመው ይህንንም መፍታት ይገባል ብለዋል፡፡ ኤጀንሲው ሙሉ አህጉራዊ ተቀባይነት እንዲኖረው ቢያንስ 35 አገራት ውሉን ማፅደቅ እንደሚኖርባቸው ጠቁመው እስካሁን ውሉን ያፀደቁት ግን 31 አገራት ብቻ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የኤጀንሲው ስምምነት እንዲፋጠንና አስተማማኝ የፈንድ ምንጭ እንዲኖርም ጥሪ አቅርበዋል። በአፍሪካ ሕብረት የኤጀንሲው ልዩ መልዕክተኛ ሚሼል ሲዲቤ በበኩላቸው፤ የአፍሪካ መድኃኒት ኤጀንሲ የአፍሪካን የጤና ዘርፍ የቁጥጥር ሉዓላዊነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጸዋል።   የአፍሪካ መድኃኒት ኤጀንሲ (AMA) ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆንና የአህጉሪቱን የቁጥጥር ሥርዓት ወደ ላቀ ደረጃ እንዲያሸጋግር፣ አህጉራዊ ውሳኔዎችን በየሀገራቱ ሕግ ውስጥ ማካተት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ይህም እስካሁን የተመዘገቡ ስኬቶችን ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመለወጥና ግልጽነት ያለው የቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችል አመልክተዋል፡፡ ኤጀንሲው ሙሉ ለሙሉ ወደ ሥራ ሲገባ እንደ ኮቪድ-19 ያሉ ወረርሽኞችና ድንገተኛ የጤና እክሎች በሚከሰቱበት ወቅት፣ በአህጉራዊ ትብብር አማካኝነት ፈጣንና የተቀናጀ ምላሽ ለመስጠት ያስችላል ተብሎ ይጠበቃል።
በኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በተሰሩ ሥራዎች የተገልጋይን እርካታ መጨመር ተችሏል
Feb 14, 2026 78
አዳማ ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በተሰሩ ሥራዎች የተገልጋይን እርካታ መጨመር መቻሉን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወሉ አብዲ አስታወቁ። እየተካሄደ በሚገኘው የጨፌ ኦሮሚያ 6ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ጉባኤ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወሉ፤ ለጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት የክልሉ መንግስት በየደረጃው አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በሰራው ሥራ ተጨባጭ ውጤት እየመጣ ነው። በተለይም አገልግሎቶችን ወደ ተጋልጋዩ ማህበረሰብ ለማቅረብ ይቻል ዘንድ አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት ተዘርግቶ ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።   በዚህም ከ7 ሺህ በላይ ቀበሌዎችን በማዋቀር 54 ሺህ አመራር እና ባለሙያ መመደቡን ጠቅሰው ምቹ የሥራ ቦታም ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል ብለዋል። በከተሞችም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተግባራዊ በማድረግ በርካታ አገልግሎቶች በአንድ ቦታ በቴክኖሎጂ ታግዘው እየተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። ቀድመው አገልግሎት መስጠት በጀመሩ አምስት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ውስጥ ከ400 ሺህ በላይ የክልሉ ነዋሪዎች አገልግሎት ማግኘታቸውንም አስረድተዋል። እስካሁን በክልሉ በከተሞችም ሆነ በገጠር በተሰሩ ሥራዎች የተገልጋዩ እርካታ እየጨመረ መምጣቱን ማወቅ ተችሏል ሲሉም አቶ አወሉ አክለዋል።   በጨፌው የክልሉ መንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ ከፍያለው ተፈራ፣ በክልሉ አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን የተሰሩ ሥራዎች ተጨባጭ ለውጥ አምጥተዋል ብለዋል። በተለይም የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን እንዲቀበሉ የክልሉ ህዝብ ከመንግስት ጋር በቅርበት በመስራቱ በርካታ ታጣቂዎች ወደ ሰላም መመለሳቸውን አስታውሰዋል። በጥፋት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ወደ ሰላም እንዲመጡ የክልሉ መንግስት አሁንም በትዕግስት እንደሚጠብቅ ገልጸው፣የመንግስትን የሰላም አማራጭ ወደጎን በማለት የህዝብ ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥሉ አካላት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ይጠናከራል ብለዋል። ህዝቡም የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ የድርሻውን እንዲያጠናክር አሳስበዋል።   በተመሳሳይ ህገ ወጥ ንግድ እና ኮንትሮባንድን ለመከላከል የተቀናጀ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን እና የጨፌው አባላትም ጥረቱን እንዲያግዙ ጠይቀዋል። የክልሉ መንግስት ገንዘብ ቢሮ ሀላፊ አቶ ቶሎሳ ገደፋ፣ በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እና በጀት እንዲጠናቀቁ ክትትል እና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። በክልሉ የሚከናወኑ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎችም ፍትሃዊነትን ማዕከል ባደረገ መልኩ የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ እንዲሆኑ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ኢኮኖሚ
ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የፓን አፍሪካኒዝም ሚናዋን የሚያጎሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ነው
Feb 14, 2026 51
አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የፓን አፍሪካኒዝም ሚናዋን የሚያጎሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች መሆኑን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር ፍራንቺስካ ቤሎቤ ገለጹ። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። ኮሚሽነር ፍራንቺስካ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ ጀምሮ በአህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውታለች። የዓድዋ ድል ለአፍሪካ ነጻነት ምልክት መሆኑን ጠቁመው፤ በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ መሪ ሚናዋን ተጫውታለች ብለዋል። በተለይም አፍሪካዊያን አንድ ሆነው የሚገጥማቸውን ፈተና በትብብር እንዲወጡ መሰረት የጣለ እንቅስቃሴ ማድረጓንም ጠቅሰዋል። የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራቾች የህብረቱ መቀመጫ ኢትዮጵያ እንዲሆን መወሰናቸው ኢትዮጵያ ለተጫወተችው ሚና እውቅና የሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል። አፍሪካ እየተለወጠ ባለው ዓለም ድምጿን እና ጥቅሞቿን ለማስከበር በአንድ ላይ መቆም ይገባታል ያሉት ኮሚሽነር ፍራንቺስካ፤ መሰል ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ በጋራ መቆም እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪው መስክ ተሻጋሪ የኢንዱስትሪ ሥርዓት እየገነባች መሆኑን ጠቁመው፤ ለማህበራዊ፣ ኢኮኖሚ ልማት ወሳኝ የሆኑ የውኃ እና ኢነርጂ አቅርቦት ላይ እያከናወነች ያለው ሥራ በምሳሌነት የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል። በተለይም የውኃና የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ሥራዎች ለቀጣናዊ ትስስር ጉልህ ፋይዳ አላቸው ያሉት ኮሚሽነር ፍራንቺስካ፤ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ልማትና ቀጣናዊ ትስስር የፓን አፍሪካኒዝም ሚናዋን የሚያጎሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የቀድሞ ሊቀ መንበር ኒኮሳዛና ዲላሚኒ ዙማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በአፍሪካ የሚታሰበውን ትብብርና ብልፅግና እውን ለማድረግ የአህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን ማፋጠን እንደሚገባ ጠቁመዋል። ለዚህ ደግሞ ትብብር እና እንደ አፍሪካ ማሰብ ይገባል ያሉት ዶክተር ኒኮሳዛና፤ የአፍሪካዊያን ኩራት ከሆነው የዓድዋ ድል በህብረት መሥራትን ልንማር ይገባል ብለዋል።
በክልሉ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚረዱ ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል
Feb 14, 2026 61
ሆሳዕና፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚረዱ ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑሪዬ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ በሀላባ ዞን ከ187 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድ፣ የተንጠልጣይ ድልድይና የመስኖ አውታር ፕሮጀክት ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል፡፡   በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑሪዬ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በክልሉ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚረዱ ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል፡፡ ዛሬ የተመረቁ ፕሮጀክቶችም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ ምርትን ወደ ገበያ ለማቅረብ እንዲሁም የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ፈጥነው እንዲጠናቀቁም ድጋፍና ክትትል ይደረጋል ብለዋል።   የአካባቢው ማህበረሰብ የፕሮጀክቶቹን ደህንነት በመጠበቅ ለረዥም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ ማስቻል እንዳለበትም አሳስበዋል። የክልሉ መስኖ ተቋማት ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ካሳዬ ተክሌ በበኩላቸው የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የመስኖ አውታር የማስፋፋት ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ብለዋል።   ዛሬ በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የሲምቢጣ የመስኖ ፕሮጀክት 80 ሄክታር መሬት ማልማት የሚችል ሲሆን 320 አባወራዎችንና እማወራዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ገልጸዋል፡፡ የክልሉ ውሃ፣ መስኖ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ተወካይ ወይዘሮ አለይካ ሽኩር በበኩላቸው፣ በሀላባ ዞን ከ73 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተገንብቶ ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የቁልቢ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ከ10 ሺህ በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን አንስተዋል።   ዛሬ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ ፕሮጀክቶች የዞኑን እድገት ለማፋጠን የሚያግዙ መሆኑን የተናገሩት የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን ሁሴን ናቸው፡፡ በተለይም የመንገድ ፕሮጀክቱ ምርታማነትን ለማሳደግና ምርትን በቀላሉ ለገበያ ለማቅረብ እንዲሁም ማህበራዊ መስተጋብርን ለማጠናከር የሚረዳ ነው ብለዋል፡፡   በሃላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ሲምቢጣ ቀበሌ ነዋሪው አርሶ አደር ገረመው መሀመድ እንደገለፁት፤ የመስኖ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ይረዳል። ከዚህ ቀደም ንፁህ የመጠጥ ውሃ በአካባቢያቸው ባለመኖሩ ውኃ ፍለጋ ረጅም ርቀት ይጓዙ እንደነበር የገለጹት ደግሞ በዚሁ ቀበሌ የሚኖሩት ወይዘሮ ወሲላ ኢብራሂም ናቸው፡፡ ቀደም ሲል ከአንድ ሰዓት በላይ ተጉዘው ለመጠጥ የሚያገኙት ውሃ ንፅህናው ያልተጠበቀ በመሆኑ ለተለያየ የጤና እክል ሲዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል። ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው ውሃ ለረጅም ጊዜ ችግራቸው ምላሽ የሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።
በአፍሪካ ቀጣናዊ የንግድ ሰንሰለትን በመገንባት የአህጉሪቷን የግብርና መዋቅር ለማዘመን ዕድል እየተፈጠረ ነው 
Feb 14, 2026 60
‎አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-በአፍሪካ ቀጣናዊ የንግድ ሰንሰለትን በመገንባት የአህጉሪቱን የግብርና መዋቅር ለማዘመን ዕድል እየተፈጠረ መሆኑን የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ ገለጹ። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና (AfCFTA) እና የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (AGRA) በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የነፃ ንግድ ቀጣናው ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ እና የአግራ ፕሬዝዳንት አሊስ ሩህዌዝ ፈርመዋል። አጋርነቱ ቀጣናዊ የንግድ ሰንሰለትን በመገንባት የአፍሪካን የግብርና መዋቅር ለማዘመን ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ተጠቁሟል። አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ እንደገለጹት፣ አፍሪካ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በምግብ ዋስትና እጥረት አጋጥሟታል። አህጉሪቱ ጥራጥሬዎችን ጨምሮ በርካታ የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ ከውጭ የምታስገባ መሆኗን ጠቅሰው፣ ይህ አካሄድ መቀየር እንዳለበት አሳስበዋል። ከስምምነቱ ዋና ዋና ዓላማዎች መካከልም የንግድ መሰናክሎችን ማስወገድ፣ ወጪን መቀነስ እንዲሁም የእውቀትና የቴክኖሎጂ ቅንጅት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ የሚያደናቅፉ አሰራሮችን በማቃለል ምርቶች በቀላሉ እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ አፍሪካ ለምግብ ግዢ የምታወጣውን የውጭ ምንዛሬ ወጪ መቀነስ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም የአግራን ቴክኒካዊ ክህሎትና የፖሊሲ እውቀት ከነፃ ንግድ ቀጣናው የንግድ መሳሪያዎች ጋር በማጣመር ውጤት ማምጣት ይገባል ብለዋል። ላለፉት ሦስት ዓመታት ሁለቱ ተቋማት በጋራ በርካታ ስራዎችን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ጠቅሰው፤ ዛሬ ስምምነቱን ይፋ የማድረግ መርሃ ግብር መከናወኑን አብራርተዋል። ስምምነቱ የምግብ ዋስትና ችግርን ለመፍታት የሚያስችል የሦስት ዓመት የሥራ እና የድርጊት መርሃ ግብርን የያዘ ነው ብለዋል። የአግራ ፕሬዝዳንት አሊስ ሩህዌዝ በበኩላቸው፣ ስምምነቱ በፖሊሲ ደረጃ የታለሙ ትልሞችን ወደ አነስተኛ አርሶ አደሮች በማውረድ ተግባራዊ ውጤት እንደሚያመጣ ገልጸዋል። ስምምነቱ በበርካታ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩር ጠቁመው፤ በተለይም የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል የግብርና ሥርዓት መገንባት፣ የምግብ ሥርዓቱን ከድርቅና ከጎርፍ አደጋዎች መከላከል እንዲሁም የግብርና ማቀነባበሪያዎችን ከንግድ ሰንሰለቱ ጋር በማገናኘት ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ በስምምነቱ መርሐ ግብር የአፍሪካ የአረንጓዴ አብዮት ጥምረት (AGRA) የቦርድ ሊቀ መንበር የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ተገኝተዋል።
የአፍሪካን የፋይናንስ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ አህጉራዊ ተቋማትን ማጠናከር ይገባል - የጋና ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ
Feb 14, 2026 61
አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካን የፋይናንስ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የአህጉሪቱን የፋይናንስ ተቋማት ማጠናከር እንደሚገባ የጋና ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ የፋይናንስ ተቋማት ሻምፒዮን ጆን ማሃማ ገለጹ። ከ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን፣ "አጀንዳ 2063ን በገንዘብ ለመደገፍ የአፍሪካን የፋይናንስ መዋቅር ማጠናከር" በሚል መሪ ሃሳብ የአፍሪካ ባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማት ሕብረት የውይይትና የትብብር ስምምነት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል። ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ በዚሁ ወቅት፤ የአፍሪካ የፋይናንስ ሉዓላዊነት በንድፈ ሃሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባር የአህጉሪቱ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ የገንዘብ ተቋምን (AMI) እስከ መስከረም 2026 ዓ.ም ድረስ ወደ ሥራ ለማስገባት አባል ሀገራት ረቂቅ ሕጉን እንዲያጸድቁና ማዕከላዊ ባንኮች አስፈላጊውን በጀትና የሰው ኃይል እንዲመድቡ ኮሚሽኑ ከአፍሪካ ማዕከላዊ ባንኮች ማህበር ጋር በቅንጅት እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል። የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ባንክን (AIB) ወደ ሥራ ለማስገባት ከ17 ዓመታት በፊት የቀረበው ምክረ ሃሳብ ተፈጻሚ እንዲሆንና አባል ሀገራት ስትራቴጂውን በማጽደቅ ለመሠረተ ልማት የሚሆን የፋይናንስ አቅም እንዲገነቡ አስገንዝበዋል፡፡ አፍሪካ የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት እንዲሻሻል ከመጠየቋ በፊት ቀደም ብሎ የራሷን የውስጥ ተቋማት በማጠናከር የመደራደር አቅሟን ማሳደግ እንዳለባት ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት የኢኮኖሚ ልማት፣ ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር ፍራንቺስካ ቻቹፕ ቤሎቤ በበኩላቸው፤ አህጉሪቱ ከዓለም አቀፍ ጫና ለመውጣት የራሷን የልማት አርክቴክቸር መቅረፅ እንዳለባት ገልጸዋል። የ2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የአፍሪካ የባለብዙ ወገን ፋይናንስ ተቋማት ጥምረት (AMFI) ሚና ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። የአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሳማይላ ዙባይሩ በበኩላቸው፤ አህጉሪቱ ያላትን ሀብት በአግባቡ አለመጠቀሟን አንስተዋል፡፡ ከሀብት አጠቃቀም አንጻር የጡረታ ፈንድን ለተራ ግንባታዎች ከማዋል ይልቅ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለሚፈጥሩ ኢንዱስትሪዎች ማዋል ይገባል ብለዋል። የአህጉሪቱን ከፍተኛ የወርቅ ክምችት የገንዘብ አሃድን ለማጠናከርና ለብድር ዋስትናነት የመጠቀም ባህል ሊዳብር እንደሚገባም ጠቅሰዋል። የአፍሪካ ማዕድናት በጥሬው እየወጡ የሌሎችን ሀገራት ኢንዱስትሪ በዝቅተኛ ዋጋ የሚደጉሙበት አሰራር ሊቆም እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። በአሁኑ ወቅት ከ60 ቢሊዮን ዶላር በላይ አቅም ያለው የአፍሪካ የፋይናንስ ተቋማት ጥምረት (AMFI) ተበታትኖ የሚገኘውን አህጉራዊ የፋይናንስ ሥርዓት ወደ አንድ በማምጣት ተጨባጭ እርምጃ መውሰድ እንዳለበት በመድረኩ ተመላክቷል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ዩኒቨርሲቲው ተተኪው ትውልድ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን ክህሎት እንዲያሳድግ ሚናውን እየተወጣ ነው
Feb 14, 2026 153
ሮቤ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተተኪው ትውልድ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን ክህሎት እንዲያሳድግ ሚናውን እየተወጣ መሆኑን ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው ከሮቤ ከተማ የተለያዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተውጣጥተው ባለፉት አራት ወራት በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ ትምህርት መስኮች ላሰለጠናቸው ተማሪዎች ዕውቅና ሰጥቷል። በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ብርሀነመስቀል ጠና (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ተቋሙ የአካባቢውን ማህበረሰብ ፍላጎትና ችግር መሰረት ያደረጉ ምርምሮችና የማህበረሰብ አገልግሎቶችን እያከናወነ ነው።   ዩኒቨርሲቲው ከስቴም ፓዎር ድርጅት ጋር በመተባበር ከዚህ በፊት የከፈተው ቤተ-ሙከራ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርት ዘርፎች የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ሁነኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የተደራጀው ቤተ-ሙከራ በተለይ በሳይንስ፣ በኢንጂነሪንግና በሂሳብ የትምህርት ዘርፎች በተግባር የተደገፈ ትምህርትን በማጠናከር ሀገራዊና አካባቢያዊ ችግሮችን የሚፈታ ትውልድ ለመፍጠር ዓላማ ማድረጉን ጠቅሰዋል። በተለይ ማዕከሉ የአካባቢው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የቴክኖሎጂና የስራ ፈጠራ ዝንባሌ እንዲኖራቸውና ክህሎታቸውን እንዲያጎለብቱ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል ትምህርታቸውን የተከታተሉ ተማሪዎች በሀገር ደረጃ ዓምና በተደረገው የሳይንስ ፌር ውድድር ላይ በመሳተፍ በአንደኝነት በማጠናቀቅ ዕውቅናና ሽልማት ማግኘታቸውን በማሳያነት አስታውሰዋል። እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ቤተ-ሙከራ ተተኪውን ትውልድ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን ክህሎት በማሳደግ ሀገሪቱ ያቀደችው የ2030 ዲጂታል ኢትዮጵያን ትልም እውን ለማድረግ አዎንታዊ ሚና እንዳለውም ፕሬዚዳንቱ አመልክተዋል። ቤተ-ሙከራው የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምህንድስናና የሂሳብ ትምህርቶች የተግባር መለማመጃ ሆኖ እያገለገለ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የስቴም ፓዎር ማዕከል አስተባባሪ መምህር አብደላ አማን ናቸው።   የሳይንስ ቤተ-ሙከራው ተማሪዎች በንድፈ-ሀሳብ የተማሩትን በተግባር እንዲያጎለብቱ የሚያስችል መሆኑንም አመልክተዋል። በዩኒቨርሲቲው እውቅና ካገኙ ተማሪዎች መካከል የሮቤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ እንደገና አበባ፣ ከዩኒቨርሲቲው ማዕከል ያገኘውን እውቀት በመጠቀም ዲጂታል ትምህርትን ለማሳለጥ የሚያግዝ መተግበርያ በማበልጸግ በሀገር ደረጃ ተሸላሚ መሆኑን ነው የገለጸው።   በዩኒቨርሲቲው የተሰጣት ተግባር ተኮር ሥልጠና ቀደም ሲል የነበራትን የሳይንስና ፈጠራ ቴክኖሎጂ ዝንባሌን ይበልጥ ለማጠናከር ረድቶኛል ያለችው ደግሞ የጋለማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሳራ መሐመድቃዲ ናት። በዩኒቨርሲቲው የተደራጀው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል የዛሬዎችን ጨምሮ 350 ተማሪዎችን በዘርፉ አሰልጥኖ እውቅና ሰጥቷል።
ኢትዮጵያ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም በዝግጅት ላይ ትገኛለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Feb 14, 2026 98
አዲስ አበባ፤ የካቲት 7/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዘርፍ ያላትን ልምድ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም በዝግጅት ላይ መሆኗን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ቃል በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በመክፈቻው መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በሚል ስትራቴጂ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። ዜጎችን ማዕከል ያደረገ የዲጂታል መሠረተ ልማት እየተገነባ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም ፋይዳ የተሰኘው ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ከክፍያ ሥርዓቶችና ከመረጃ ልውውጥ አውታሮች ጋር በመቀናጀቱ ዜጎች ቀልጣፋና ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት እንዲያገኙ እያስቻለ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2020 በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነውን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ማቋቋሟን አስታውሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ኢትዮጵያ በመደመር ፍልስፍና ላይ የተመሠረተና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዩኒቨርሲቲ ለመክፈት ዝግጅት ላይ መሆኗን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው የሰውን ልጅ እሴቶች ከማሽን ኢንተለጀንስ ጋር የሚያስተሳስር፣ አካባቢያዊ ሁኔታዎችን ከዓለም አቀፍ ሳይንሳዊ ምርምር ጋር የሚያቀናጅ እንዲሁም አፍሪካ በቴክኖሎጂው ዘመን የራሷን አዎንታዊ አሻራ እንድታሳርፍ የሚያስችል እንደሚሆንም አብራርተዋል። ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር የአገልግሎት አሰጣጥን ከማዘመን ባለፈ፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን በማፋጠን አፍሪካ በዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መድረክ ያላትን ተሳትፎ እንደሚያጠናክር ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል፡፡
በአፍሪካ የዲጂታል መሰረተ ልማትን በማስፋፋት አፍሪካን ከዓለም ገበያ ጋር ለማስተሳሰር ትብብራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ
Feb 13, 2026 100
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦በአፍሪካ የዲጅታል መሰረተ ልማትን በማስፋፋት አፍሪካን ከዓለም ገበያ ጋር ለማስተሳሰር ትብብራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ገለጹ፡፡ ሁለተኛው የጣሊያን-አፍሪካ ስብሰባ በአዲስ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ማዕከል መካሄድ ጀምሯል፡፡ ኢትዮጵያና ጣሊያን ሁለተኛውን የአፍሪካ ጣሊያን ጉባዔ በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን፤ የሀገራችንን የዲፕሎማቲክ የስበት ማዕከልነቷን ዳግም የሚያረጋግጥ፣ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ያላትን ቦታ በጉልህ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚያሳይ ነው።   በመርሃ ግብሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንትና የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር ጆአዎ ሎሬንዞ፣ የተመድ ዋና ጸሀፊ አቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሀሙድ አሊ ዩሲፍ እና የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ተገኝተዋል፡፡ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ጣሊያንና አፍሪካ በተለያዩ መስኮች በትብብር እየሰሩ ነው፡፡ የጣሊያንና አፍሪካ የጋራ ግቦችን ለማሳካት በኢነርጂ፣በትምህርትና ስልጠና፣ በጤና በዲጂታልና በመሰረተ ልማት ግንባታ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በታዳሽ ሀይል፣ በአረንጓዴ ልማት ሽግግር፣ በምግብ ዋስትና እና መሰል መስኮች ያለው ትብብር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ የዲጂታል መሰረተ ልማትን በማስፋፋት አፍሪካን ከዓለም አቀፉ ግብይት ለማስተሳሰር በጋራ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል፡፡ ጣሊያን በመንግስትና በግሉ ዘርፍ ትብብር በሀይል መሰረተ ልማት ላይ በትኩረት እየሰራች መሆኑን ገልጸው፤ ከአፍሪካ ጋር በትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ትብብራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ጠንካራ የጤና ስርዓት ለመገንባት የላቀ ትብብር አለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሯ፤ ትብብሩ ጠንካራና ተደራሽ የጤና ስርዓት መገንባት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ በኢንዱስትሪ ልማትና በግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ላይ በጋራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፤ በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ላይ ልዩ ትኩረት ተደርጓል ብለዋል፡፡ በማቲ ፕላን መሰረት ሁሉም ፕሮጀክቶች ትምህርትና ስልጠና ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን በማንሳት፤ ትኩረታቸው የአፍሪካን ህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ጣሊያን ለሰው ሃብት ልማት ትኩረት እንደምትሰጥ በማንሳት፤ ወጣቶች በአህጉራቸው ስራ ተፈጥሮላቸው ስደትን ማስቀረት ይገባል ብለዋል፡፡
የሠመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጉላላትን አስቀርቷል
Feb 13, 2026 147
ሠመራ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የሠመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉዳያቸውን በፍጥነት በመጨረስ መጉላላትን እንዳስቀረላቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናገሩ። የሰመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፣ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሸነር መኩሪያ ኀይሌ(ዶ/ር) እና የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በተገኙበት ህዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም ተመርቆ ስራ መጀመሩ ይታወሳል። ማእከሉ ለደንበኞች የተቀላጠፈ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ በማሳደጉ ተግባሩን ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች የማስፋት ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ማዕከሉ የዘረጋው የተቀላጠፈ አገልግሎት ጊዜና ገንዘባቸውን ከብክነት በማዳን እንግልትን እንዳስቀረላቸው የሰመራ ሎጊያ ነዋሪዎች ለኢዜአ ገልጸዋል። የአገልግሎት አሰጣጡን አስመልክቶ ሀሳባቸውን ከሰጡ ተገልጋዮች መካከል የሠመራ ከተማ ነዋሪው አቶ ሀቢብ መሐመድ፤ የሰመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ መስሪያ ቤቶችን በአንድ ላይ በማግኘት በአጭር ጊዜ ጉዳያቸውን ለመጨረስ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።   ይህም ከመጉላላትና ከተጨማሪ ወጪዎች እንደታደጋቸውና ጊዜያቸውን በተገቢው እንዲጠቀሙ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል። ማዕከሉ የተለያዩ ተቋማትን አገልግሎቶች አቀናጅቶ መያዙ ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ ያሲን ሁሴን ናቸው።   ይህም በተለይም ከንግድ ፈቃድ ዕድሳት ጋር ተያይዞ ይወስድ የነበረውን ረጅም ጊዜ ማስቀረት የቻለ መሆኑን ተናግረዋል። የሠመራ ሎጊያ ነዋሪው አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ በአንድ ቦታ በመሆኑና በቴክኖሎጂ በመታገዝ አገልግሎት ማግኘት ችያለሁ ብለዋል።   የሠመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ከሊል አሊ፤ ማዕከሉ በአምስት ተቋማትና በ13 አገልግሎት ዘርፎች አገልግሎት መጀመሩን አስታውሰው አሁን አገልግሎቱ ወደ 29 ዘርፎች ማደጉን ተናግረዋል። በዚህም በሶስት ወራት ውሰጥ 7ሺህ 800 ለሚሆኑ ባለጉዳዮች አገልግሎት መሰጠቱን ገልፀዋል።   ይህም የማህበረሰቡን እንግልትን እንዲሁም ብልሹ አሰራሮችን ለመቅረፍ በማገዙ ስራውን ይበልጥ በማስፋት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ስፖርት
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች ያከብራል
Feb 13, 2026 81
ሀዋሳ ፤የካቲት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በሀገር መከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ከነገ የካቲት 7 እስከ 15 ድረስ በተለያዩ ዝግጅቶች ያከብራል። የዕዙን የምስረታ በዓል አከባበር በማስመልከት ዛሬ መግለጫ የተሰጠ ሲሆን በዓሉ በነገው እለት በሀዋሳ ከተማ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በማካሄድ መከበር እንደሚጀምር ተመላክቷል። ከተመሰረተ 65 ዓመታት ዕድሜ ያስቆጠረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ከፍተኛ ጀግንነትን የፈጸሙ ኮማንዶ፣ አየር ወለድና ልዩ የጸረ ሽብር ሀይሎችን ሲያሰለጥን ቆይቷል። እነዚህን የሀገር ባለውለታዎች ያፈራው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የመስረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ነገ በሀዋሳ ከተማ ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በወንዶችና በሴቶች ታዋቂ አትሌቶችን ጨምሮ ከሀዋሳና ከአጎራባች ከተሞች የተውጣጡ ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች የሚሳተፉበት የሩጫ ውድድር እንደሚካሄድ ታውቋል። በሩጫ ውድድሩ ላይ ለመሳተፍም አትሌቶች ወደ ሀዋሳ ከተማ መግባታቸውን በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኢንተርናሽናል ኮርስ ሜጀረር ተሾመ በቀለ ገልጸዋል። በዚህ ውድድር 202 ወንድና 80 ሴት ታዋቂ አትሌቶች እንደሚሳተፉ ገልጸው በአማራ፣ ኦሮሚያና ሲዳማ ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ ክለቦች እና በግል የሚወዳደሩ አትሌቶች ይሳተፋሉ ብለዋል። በውድድሩ በሁለቱም ጾታ ከአንደኛ እስከ አምስተኛ ለሚወጡ አትሌቶች እንደየደረጃቸው የገንዘብ ሽልማት እንደሚሰጥም አመልክተዋል። ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ሀዋሳ ሱሙዳ አደባባይ ማድረጉንም ተጠቁሟል።   የሲዳማ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ አቶ ወሰንየለህ ስምኦን በበኩላቸው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በድምቀት እንዲከበር ክልሉ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅቶች አድርጓል ብለዋል። መላው የሲዳማ ህዝብና የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች የበዓሉ ታዳሚዎችን በእንግዳ ተቀባይነት ባህል ተቀብሎ ሊያስተናግድ እንደሚገባም አቶ ወሰንየለህ አሳስበዋል።  
በስፔን ጥሎ ማለፍ የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ ጨዋታ አትሌቲኮ ማድሪድ ባርሴሎናን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ
Feb 13, 2026 124
አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፦ በስፔን ጥሎ ማለፍ (ኮፓ ዴል ሬይ) የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ ጨዋታ አትሌቲኮ ማድሪድ ባርሴሎናን 4 ለ 0 ረቷል። ማምሻውን በዋንዳ ሜትሮፖሊታኖ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አንቶዋን ግሪዝማን፣ ጁሊያን አልቫሬዝ፣ አዲስ ፈራሚው አዴሞላ ሉክማን እና የባርሴሎናው ግብ ጠባቂ ኤሪክ ጋርሺያ በራሱ ላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በመጀመሪያው አጋማሽ ፍጹም የጨዋታ ብልጫ የወሰደው አትሌቲኮ ማድሪድ በ45 ደቂቃ አራት ግቦችን አስቆጥሯል። የባርሴሎናው ተከላካይ ኤሪክ ጋርሺያ በ86ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ባርሴሎና በሁለተኛው አጋማሽ ወደ ጨዋታው ለመመለስ ቢሞክርም አትሌቲኮ ማድሪድ ውጤቱን ማስጠበቅ ችሏል። አትሌቲኮ ማድሪድ ወደ ፍጻሜ የማለፍ እድሉን አስፍቷል። አስደንጋጭ ሽንፈት ያስተናገደው ባርሴሎና ውጤቱን የመቀልበስ ከባድ ፈተና በመልሱ ጨዋታ ይጠብቀዋል። የመልሱ ጨዋታ የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በካምፕ ኑ ስታዲየም ይደረጋል። ትናንት በተደረገው ሌላኛው የስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ ጨዋታ ሪያል ሶሳዬዳድ ከሜዳው ውጪ አትሌቲኮ ቢልባኦን 1 ለ 0 አሸንፏል። የመልሱ ጨዋታ የካቲት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ባርሴሎና የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ነው።
አካባቢ ጥበቃ
የበልግ እርሻን ቀድመው የሚጀምሩ አካባቢዎች በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረውን የርጥበት ሁኔታ በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል
Feb 13, 2026 75
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የበልግ እርሻን ቀድመው የሚጀምሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የሚኖረውን የርጥበት ሁኔታ በአግባቡ እንዲጠቀሙበት ኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ከየካቲት 4 እስከ የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አሥር ቀናት የሚኖረውን የአየር ሁኔታ ትንበያ ይፋ አደርጓል፡፡ ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፣ የበልግ እርሻ እንቅስቃሴ ቀድመው የሚጀምሩ አካባቢዎች የሚገኘውን እርጥበት በአግባቡ እንዲጠቀሙበት አሳስቧል። በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በደቡብ ምዕራብ፣ በስምጥ ሸለቆና አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር ገልጿል፡፡ በተጨማሪም በመካከለኛውና በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የደመና ሽፋን እንደሚጨምር አመልክቷል፡፡ በጋምቤላ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በሰሜን ምስራቅና በደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች የቀኑ ከፍተኛ የሙቀት መጠን ከ32 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ሆኖ እንደሚቀጥል ተቋሙ ጠቁሟል። በቀጣይ የሚኖረው የአየር ሁኔታ ለቋሚ ተክሎች የተሻለ እድገት እንዲያገኙ ያግዛል፣ ለአርብቶ አደሩ የግጦሽ ሳርና የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማሻሻል ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር እንዲሁም ለበልግ እርሻ ማሳን ቀድሞ ለማዘጋጀትና የአፈር ውስጥ እርጥበትን ለማሻሻል እንደሚረዳም ጠቅሷል፡፡ ሆኖም የእርጥበት መጠን ለሰብል ዝርያ የሚበቃ ባለመሆኑና ደረቅ አየር ሁኔታም ስለሚስተዋል አርሶ አደሩ ይህንን ተገንዝቦ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል። በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በአብዛኞቹ ተፋሰሶች ላይ ደረቃማ የአየር ሁኔታ የሚጠበቅ በመሆኑ የገጸ-ምድር ውሃ ፍሰት ሊቀንስ እንደሚችል ተገልጿል። በተለይም በባሮ አኮቦ፣ በኦሞ ጊቤ፣ በስምጥ ሸለቆና በገናሌ ዳዋ ተፋሰሶች ላይ ዝቅተኛ የውሃ ፍሰት እንደሚኖር የተገለጸ ሲሆን በውሃ አጠር አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ውሃን ከብክነትና ከብክለት እንዲከላከሉ፣ እንዲሁም አማራጭ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል። በሚቀጥሉት አሥር ቀናት ለበልግ እርሻ ዝግጅትና ለቋሚ ተክሎች እንክብካቤ አመቺ ቢሆኑም ለዝርያ የሚበቃ ዝናብ ባለመኖሩና የውሃ መጠን ሊቀንስ ስለሚችል አስፈላጊው ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ ተመላክቷል።  
ኢትዮጵያ በውኃ ዘላቂነትና ተደራሽነት ረገድ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች ነው
Feb 12, 2026 135
አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በውኃ ዘላቂነትና ተደራሽነት ረገድ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች መሆኗን የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ ምክር ቤት ሴክሬታሪያት ገለጸ።   የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ ምክር ቤት ሴክሬተሪያት ኃላፊ ዊሊያም ካሪው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት እያሳየ ያለው የአመራር ሚና ለአፍሪካ ኅብረት እጅግ መሰረታዊ መሆኑን ጠቁመዋል። የኅብረቱ አባል ሀገራት በማንኛውም አባላት ዘንድ የተዘረጉ መልካም ተሞክሮዎችንና ፖሊሲዎችን በአርዓያነት መጠቀም እንዳለባቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት ለዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ተደራሽነት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ፖሊሲዎችንና አሠራሮችን መዘርጋቱን ገልጸው፤ ይህም ለሌሎች የአፍሪካ ኅብረት አባል ሀገራት መልካም ተሞክሮ መሆኑን አስታውቀዋል። በተወሰዱ የፖሊሲ ለውጦችና ቆራጥ የአመራር ሰጭነት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችውን ስኬትም አድንቀዋል። ይህ ትልቅ ቁጥር መሆኑን ጠቁመው፤ የአመራርና ትክክለኛ ፖሊሲዎች ውጤት መሆኑን አስረድተዋል።  
የተፋስስ ልማት ሥራ የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርታማነትን በማሳደጉ አጠናክረን ቀጥለናል
Feb 12, 2026 107
ወልቂጤ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፡-የተፋሰስ ልማት ሥራ የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርታማነትን እያሳደገ በመሆኑ ዘንድሮም አጠናክረው መቀጠላቸውን የጉራጌ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ፡፡ አርሶ አደሮቹ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች የአፈር ለምነትን በመጠበቅና የተጎዱ መሬቶች እንዲያገግሙ በማድረግ ምርታማነትን እያሳደገ በመሆኑ ዘንድሮም ልማቱን ማጠናከራቸውን ገልጸዋል። በጉራጌ ዞን የእኖር ኤነር መገር ወረዳ አርሶአደር በደዊ ታቅንዳ በተፋሰስ ልማት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ መጀመሩ በጎርፍ ተጠርጎ ይወሰድ የነበረ ለም አፈር ጥቅም ላይ ለማዋል አስችሏል ብለዋል።   ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ሥራዎች የተራቆቱ መሬቶች ማገገማቸው እና የደረቁ ምንጮች ዳግም መፍለቃቸው የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውን ተናግረዋል። በዚህም በዘንድሮ የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ሥራ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን ጠረጴዛማ የእርከን ልማት ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላኛው የእዣ ወረዳ አርሶ አደር ወይዘሮ ሙርጋት ታቅንዳ በበኩላቸው ባለፉት ተከታታይ ዓመታት የተከናወነው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ መሬታቸውን ከመሸርሸር መታደጉን ገልጸዋል።   የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ የመሬት ለምነትን በመመለስ ምርታማነትን እያሳደገ በመሆኑ በዘመቻው በንቃት እየተሳተፉ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ የተጎዱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙና ምርታማነታቸው እንዲጨምር ማድረጉን የተናገሩት ሌላኛው የእኖር ወረዳ አርሶ አደር መህዲ ደሊል ናቸው። የተፋሰስ ልማት ሥራው እየተመናመኑ የነበሩ የደንና የውኃ ሀብቶች እንዲመለሱ ማስቻሉንም ገልፀዋል ።   የለሙ አካባቢዎችን ከሰውና ከእንስሳት ንኪኪ በመጠበቅ ለመኖ ልማትና ለንብ ማነብ ሥራ በማዋል ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እያስቻሉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በበኩላቸው እንዳሉት ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራዎች ውጤት ተመዝግበዋል። በተለይም ተዳፋታማ በሆኑ አካባቢዎች ጠረጴዛማ እርከን በመስራት ከምርት ውጭ የነበሩ መሬቶች አገግመው በተለያዩ ሰብሎች እንዲለማ ከመደረጉ ባለፈ ለንብ ማነብ ሥራ እየዋሉ መሆኑን ገልጸዋል።   የደረቁ ምንጮችና በጎርፍ በመሸርሸር የተጎዱ መሬቶች ማገገማቸው የግብርና ምርትና ምርታማነትን እያሳደገው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶች አርሶ አደሩን ተጠቃሚ በማድረጋቸው በዘንድሮ ተፋሰስ ልማት የወጣቶችና የሴቶች ተሳትፎ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ገልጸዋል። በዘንድሮ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራ በዞኑ በ23 ሺህ ተፋሰሶች ላይ 88 ሺህ 581 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።  
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በአፍሪካ የውሃ ዋስትናን ለማረጋገጥ አርዓያነት ያለው ተግባር ነው
Feb 9, 2026 207
አዲስ አበባ፤ የካቲት 2/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራና ተፋሰስ ልማት ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በአፍሪካ የውሃ ዋስትናን ለማረጋገጥ አርዓያነት ያለው ተግባር ነው ሲሉ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በአፍሪካ ሕብረት የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ባህል ምክር ቤት "የአጀንዳ 2063 ግቦች ለማሳካት ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ" የሚለውን የ39ኛው የሕብረቱን መሪ ቃል በተመለከተ የሲቪል ማህበረሰብ ቅድመ ስብሰባ አካሂዷል፡፡   የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በአፍሪካ ከ400 ሚሊየን በላይ ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር ይገጥማቸዋል፡፡ በአህጉሪቱ ከ700 ሚሊየን በላይ ዜጎች በተለይም ወጣቶች፣ ሴቶችና የገጠር ነዋሪዎች የንጽህና አጠባበቅ (ሳኒቴሽንና ሀይጅን) ጉድለት ችግር እንደሚያጋጥማቸው ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረትም የአጀንዳ 2063 አንዱ ግብና የዘንድሮው ዓመት መሪ ሀሳብ ያደረገውም ውሃ የዜጎች መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ ነው ብለዋል፡፡ በአህጉሪቷ ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና የአካባቢ ንጽህናን ማረጋገጥ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማስመዝገብ እና ውሃ ወለድ በሽታን ለመከላከል ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ የውሃ ሀብታችን የኢኮኖሚያችን አቅም፣ የህልውናችን መሰረት ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታተ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ትብብር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት ዘላቂ የውሃ ሀብት ልማትን ለማረጋገጥ ተጨባጭ የተግባር ውጤት ማስመዝገቧን ገልጸው፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ተክላለች ብለዋል፡፡ እነዚህ የተተከሉ ችግኞች የፅድቀት መጠንም ከ90 በመቶ በላይ ሲሆን፤ በዚህ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ከፍተኛ መጠን ያለው ውሃ ማዳን እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡   በመሆኑም ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ እና ተፋሰስ ልማት ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች አፍሪካውያን በትብብር የንጹህ መጠጥ ውሃና ንጽህናን ማረጋገጥ እንደሚችሉ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የወንዝ ዳርቻ እና ኮሪደር ልማት ስራ በአዲስ አበባ ከተማ ጀምራ ወደ ተለያዩ ክልሎች ማስፋቷን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ይህም የወንዞችን ውበትና የውሃ ንጽህናን መጠበቅ አስችሏል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ የገጸ ምድርና ከርሰ ምድር የውሃ ሀብት እንዳይበከል አስፈላጊውን የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ማከናወን እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ በመሆኑም እንደ አፍሪካ በጋራ በመተባበር ከቻልን አንዳችን ለአንዳችን በረከት እንሆናለን፤ ንጹህ የከርሰ ምድር ውሃ ይኖረናልም ብለዋል፡፡  
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባለብዙ ወገን አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለጹ
Feb 13, 2026 100
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ የፀጥታው ምክር ቤት ውክልናን ጨምሮ የባለብዙ ወገን አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታወቁ። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከጉባኤው አስቀድሞ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት፣ ዘላቂ ልማትና ሁሉን አቀፍ ኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ላይ ያተኮረ ነው። በተለይም የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ እሴት መጨመርና መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ለእድገት፣ ለስራ ፈጠራ እና ለዘላቂ መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ ተነስቷል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የህብረቱ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አጋርነት ኢ-ተገማች በሆነው የዓለም ሁኔታ ውስጥ ሰላም፣ ደህንነትና ዘላቂ አጋርነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የአፍሪካ ህብረት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባለብዙ ወገን ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኑን ገልጸው አፍሪካ በዓለም ሰላም፣ ደህንነትና የባለብዙ ወገን ስርዓት ሪፎርም ወሳኝ ሚና እንዳላት ተናግረዋል። በውይይቱ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት አስቸኳይ ሪፎርም እንደሚያስፈልገውና አፍሪካ በምክር ቤቱ ቋሚ ውክልና ማግኘት እንደሚገባት ተነስቷል። ባለስልጣናቱ ህብረቱ እና ተመድ የዓለም የፋይናንስ ስርዓት እንዲሻሻልና አፍሪካ ፍትሃዊ የፋይናንስ አቅርቦት እንድታገኝ የጀመሩትን የጋራ ስራ አጠናክረው ለመቀጠል መስማማታቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
አጀንዳ 2063: የ50 ዓመቱ የአፍሪካ እቅድ 
Feb 13, 2026 244
.አጀንዳ 2063 ‘የምንፈልጋትን አፍሪካ ‘ በሚል መሪ ሀሳብ አፍሪካ ለ50 ዓመት (ከእ.አ.አ 2013 እስከ 2063) የምትመራበትን እቅድ የያዘ ማዕቀፍ ነው። .አጀንዳው ለመጀመሪያ ጊዜ ውይይት የተደረገበት እ.አ.አ በ2013 በአዲስ አበባ በተካሄደው 21ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ(ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት 50ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የተከበረበት ነው)። .አጀንዳ 2063 እ.አ.አ በ2015 በአዲስ አበባ በተካሄደው 24ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ውይይት ተደርጎበት አባል አገራቱ አጽድቀውታል። .የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ አፍሪካ ሕብረት) አፍሪካ ከአፓርታይድ ስርዓት ለማላቀቅና የፖለቲካ ነጻነት እንድታገኝ ሲያደርግ የነበረው ትግል ለአጀንዳ 2063 አጀንዳ መጠንሰስ ምክንያት እንደሆነ ይገለጻል። .አጀንዳ 2063 በአፍሪካ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ የሆነ ልማት ማምጣት እንዲሁም በፓን አፍሪካኒዝምና የአፍሪካ ሕዳሴ ራዕይ ስር አንድነቷን የጠበቀች፣ የራስን እድል በራስ የምትወስን፣ነጻ የሆነች፣የተለወጠችና የበለጸገች አፍሪካ የመፍጠር ግብ እንዳለው የአፍሪካ ሕብረት በድረ ገጹ ላይ ያሰፈረው መረጃ ያሳያል። .አጀንዳ 2063 የአፍሪካን ሁሉን አቀፍና ዘላቂ የልማት ግቦችን ያሳካል ተብሎ የታመነበት የአህጉሪቷ ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ ሲሆን፤አፍሪካን በዓለም መድረክ ተጽእኖ ፈጣሪ የማድረግ ራዕይ ያለው ነው። አጀንዳ 2063 ሰባት ግቦች ሳይሆን ሰባት አላማዎች፣20 ግቦችና 15 ፕሮጀክቶች ያሉት ነው የአጀንዳ 2063 ሰባት አላማዎችና ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫዎች አጀንዳ 2063 ‘የምንፈልጋትን አፍሪካ ‘ በሚል መሪ ሀሳብ አፍሪካ ለ50 ዓመት (ከእ.አ.አ 2013 እስከ 2063) የምትመራበትን እቅድ የያዘ ማዕቀፍ ነው። አጀንዳ 2063 ሰባት አላማዎችና ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫዎች አሉት። እነሱም፦ 1. ሁሉን አቀፍ በሆነ እድገትና ዘላቂ ልማት የበለጸገች አፍሪካን መፍጠር 2. በፓን አፍሪካኒዝም እሳቤዎችና በአፍሪካ ሕዳሴ ራዕይ አማካኝነት የተሳሰረችና ፖለቲካዊ አንድነት ያላት አህጉርን እውን ማድረግ 3. አፍሪካን መልካም አስተዳደር የሰፈነባት፣ የሰብአዊ መብቶችና የሕግ የበላይነት የሚከበርባት፣ ፍትሕ የነገሰባትና ዴሞክራሲያዊ አህጉር ማድረግ 4 .ሰላሟንና አንድነቷን የጠበቀች አፍሪካን መፍጠር 5.ጠንካራ የባህል ማንነት፣ የጋራ ቅርስና እሴቶች ያሏት እንዲሁም ጠንካራ ማህበረሳባዊ የሞራል መሰረት የፈጠረች አፍሪካን ማየት 6. አፍሪካ ልማቷ ዜጎችን ማዕከል ያደረገ፣ የአፍሪካን ሕዝብ በተለይም የወጣቶችና ሴቶችን አቅም የሚጠቀምና ለሕጻናት ክብካቤ ትኩረትን የሰጠ እንዲሆን ማድረግ 7. ጠንካራ፣ አንድነቷን የጠበቀች፣ የማትበገርና በዓለም መድረክ ተጽእኖ ፈጣሪና አጋር የሆነች አፍሪካን መፍጠር ናቸው። የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሄደው 39ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ በአጀንዳ 2063 አፈጻጸም ትግበራ ላይ እንደሚመክር የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
የኮሞሮስ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሶማኒ እና የሌሴቶው ንጉስ ሌትሴ ሳልሳዊ በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገቡ
Feb 11, 2026 164
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2018(ኢዜአ)፦ የኮሞሮስ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሶማኒ እና የሌሴቶው ንጉስ ሌትሴ ሳልሳዊ በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።   ፕሬዚዳንቱ እና ንጉሱ ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) እና የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በተያያዘ ዜና የጋምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት መሐመድ ጃሎው በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል። ምክትል ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ አቀባበል አድርገውላቸዋል። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ ይካሄዳል።
48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀመረ
Feb 11, 2026 168
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2018(ኢዜአ)፦ 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ስብሰባው “ዘላቂ የውሃ ኑረትና ንጽህና ስርዓት ለአጀንዳ 2063 ስኬት” በሚል መሪ ሀሳብ ይደረጋል። የአፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ዲፕሎማቶችና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል። በስብሰባው የሚሳተፉ የአፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ሚኒስትር ዴኤታዎች እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል። ምክር ቤቱ በጥር ወር 2018 ዓ.ም 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ በተወያየባቸው አጀንዳዎች ላይ ምክክር ያደርጋል። የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤቱ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል። የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ እስከ ነገ ይቆያል።
ሐተታዎች
   የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 40
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን።   የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው።   የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል።   የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት።   የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 532
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ።   በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 871
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 802
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 920
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 866
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 1441
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3744
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3407
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2240
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8040
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6529
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60210
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54176
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34783
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32344
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27594
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26578
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26107
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25883
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60210
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54176
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34783
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32344
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ ዐሻራ ከዓድዋ - እስከ አፍሪካ ኅብረት
Feb 14, 2026 99
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የፖለቲካ፣ የታሪክ እና ዲፕሎማሲ ምኅዳር ውስጥ ልዩ ስፍራ እና ተጽዕኖ ያላት ሀገር ናት። የጥንታዊ ሥልጣኔዎች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ፤ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ የአፍሪካ ሀገር ከመሆኗ ባሻገር ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ መስፋፋት ትልቅ ሚና ተጫውታለች። ይህንም ታሪክ ይዘክራል። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ዛሬ ይጀመራል አይበገሬነት፣ ሉዓላዊነት እና የፓን አፍሪካ መንፈስ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ካሳረፈቻቸው ዐሻራዎች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። በዘመናዊው ዓለምም በአፍሪካ አጀንዳዎች ላይ ወሳኝ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነጻነት እና ማንነት ተምሳሌት ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1896 በዓድዋ ጦርነት በጣሊያን ኃይሎች ላይ የተቀዳጀችው ድል በአፍሪካ እና በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ የሚሰጠው ነው።   አብዛኛው የአፍሪካ አኅጉር በቅኝ ግዛት ውስጥ በነበረበት ወቅት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ድል ሉዓላዊነቷን ከማስጠበቅ ባለፈ በአፍሪካ እና በአፍሪካ ዳያስፖራ የነጻነት ትግሎች እንዲቀጣጠሉ አድርጓል። በተለይም ከ20ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ ለነበሩ እንቅስቃሴዎች ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ይህ ታሪካዊ ዐሻራ ኢትዮጵያን የጥቁሮች ኩራት፣ ትግል እና ራስን የመቻል ምልክት እንድትሆን አስችሏታል። የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና አዲስ አበባ የአፍሪካ ኅብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ ኢትዮጵያ የአኅጉሪቷ የዲፕሎማሲ ማዕከል ሆና እንድትቀጥል አስችሏል። እ.አ.አ በ1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ኅብረት) ታሪካዊ ምሥረታ የተካሄደው በኢትዮጵያ ነው። ኢትዮጵያ ከድርጅቱ መሥራች ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ይህም የአፍሪካ የጋራ የፖለቲካ ድምጽ እንድትሆን ምክንያት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሴኤ) እና ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ተቋማት የሚገኙባት ኢትዮጵያ፤ በዲፕሎማሲው ምክክር እና ውሳኔ ሰጪነት ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የበለጠ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ድምጽ ኢትዮጵያ በቅኝ አለመገዛቷ ለፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ ሥር መስደድ ወሳኝ ነው። በፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ለአፍሪካ አንድነት እና የጋራ ምላሽ አጥብቃ ስትሞግትም ቆይታለች። በአፍሪካ ኅብረት እና በተለያዩ መድረኮች ኢትዮጵያ የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን መፈታት አለባቸው የሚለውን እሳቤ ለማስረጽ አበክራ እየሠራች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተኮር መፍትሔዎች ከቃላት ባለፈ በአኅጉራዊ የትሥሥር አጀንዳዎች፣ ሰላም እና ደኅንነት ማዕቀፎች እንዲሁም የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ፈተናዎች እንዲፈቱ ድጋፏን በመስጠት ቁርጠኝነቷን አሳይታለች። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነትንም በፍጥነት አጽድቃ ወደ ሥራ ማስገባቷ የዚሁ አንድ ማሳያ ነው። ሰላም ማስከበር እና ቀጣናዊ መረጋጋት ኢትዮጵያ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ስትራቴጂካዊ ሚና እየተወጣች ነው። በዚህም መሠረት ለተባበሩት መንግሥታት እና የአፍሪካ ኅብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማድረግ ከአፍሪካ ሀገራት ቀዳሚውን ድርሻ ትይዛለች።   ሶማሊያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ ግጭት ባለባቸው የአፍሪካ ሀገራት ወታደሮቿን በመላክ ለሰላም እና ደኅንነት ያላትን ሚና በተግባር ገልጣ አሳይታለች። የተባበሩት መንግሥታትም ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር እየተወጣች ላለው ሚና ምሥጋናውን ማቅረቡ ይታወቃል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሀገራት ያሉ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የተወጣችው የእርቅ እና የዲፕሎማሲ ሚናም ተጠቃሽ ነው።   የኢኮኖሚ እድገት እና ቀጣናዊ ትሥሥር ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል በዋናነት ትጠቀሳለች። በ2017 ዓ.ም ማብቂያ የተመረቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በግንባታ ላይ የሚገኘው ኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከግዙፍ መሠረተ ልማትነታቸው ባለፈ ቀጣናዊ ትሥሥር በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሚና አላቸው። ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢነርጂ የስኅበት ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል። ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት የምትሸጠው ኢነርጂ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን የሚያሳልጥ ነው። የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መንገድን ጨምሮ የመንገድ መሠረተ ልማቶች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኢትዮጵያን የቀጣናዊ ትሥሥር ማዕከል እንድትሆን እያደረጓት ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት እየተከናወነ ያለው አረንጓዴ ዐሻራም፤ ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ትብብር እና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተምሳሌት ማድረግ ችሏል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ አጀንዳ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ትገኛለች። የባህል እና የሥልጣኔ አስተዋጽዖ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ታሪክ፣ ቱባ ባህል እና ብዝኃነት መገለጫዋ ናቸው። የቋንቋ ብዝኃነት በአፍሪካ ውስጥ ገራገር የዲፕሎማሲ ኃይል (Soft Power) እንዲኖራት አስተዋጽዖ አድርጓል። የኢትዮጵያ የሀገርነት ታሪክ እና የሥልጣኔ ትርክት አፍሪካ ያሏትን ጥልቅ የታሪክ ሥሮች ይበልጥ አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የኢትዮጵያ ብዝኃ ማንነቶች፣ ሀገር በቀል ዕውቀቶች እና አስደማሚ የሥነ-ሕንጻ ሥራዎች በአፍሪካ ባህል እና ሥልጣኔ ውስጥ ያላቸው ሚና ትልቅ ነው። ኢትዮጵያ አሁንም በአፍሪካ አንድነት እና መረጋጋት ውስጥ እንደ ቁልፍ ምሰሶ ትታያለች። በአኅጉሪቱ ውስጥ ያላት ድርሻ በታሪክ ሥር የሰደደ እና አሁን ባለው ዘመን በዲፕሎማሲ፣ በሰላም ግንባታ እና ልማት ሥራ በግልጽ ጎልቶ ይታያል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የፖለቲካ መዲና እንዲሁም የአይበገሬነት እና የነጻነት ምልክት ናት። አፍሪካ አንድነቷን ለማረጋገጥ፣ የተረጋጋ አኅጉር ለመፍጠር እና በራስ ዐቅም ነገሮችን የመከወን ጉዞ ትልም ውስጥ የኢትዮጵያ ድርሻ ቁልፍ ነው።   39ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ “ዘላቂ የውኃ ኑረትና ንጽህና ሥርዓት፤ ለአጀንዳ 2063 ስኬት” በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬና ነገ በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። ጉባዔው ኢትዮጵያ አኅጉራዊ የፖለቲካ እና ዲፕሎማሲያዊ መድረክ መሆኗን ዳግም የምታሳይበት ነው።
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!!
Feb 6, 2026 229
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በያንተስራ ወጋየሁ -ዲላ ቀን ቀንን እየወለደ ጊዜ ሳያቋርጥ እንደ ዥረት መፍሰሱን አያቆምም። ትናንት አዲስ የነበረው አሮጌው የሚባልበት፣ ዛሬ አዲስ ሆኖ ነገ አሮጌ ለመባል ይሮጣል። ወቅቶች ይፈራረቃሉ፣ ይመሻል፣ ይነጋል፣ ትናንት ለዛሬ፣ ዛሬ ለነገ እንዲህ እንዲህ እየተቀባበሉ ዘመን ዘመንን እየተካ ዛሬ ላይ ተደርሷል።   በጥምር ግብርናውና በቡናው የሚታወቀው ጌዴኦ ትናንትን ሸኝቶ ዛሬን እንደ አዲስ ለመቀበል ሽር ጉድ እያለ ነው። በክረምቱ የተዘራው ሰብል ተሰብስቦ ወደ ጎተራ እንዳስገባ ጌዴኦ አዲስ ዓመቱን ‹‹ዳራሮ››ን ይቀበላል። ዳራሮ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ቂም የያዘ ቂምና ቁርሾውን የሚተውበት፣ ወጣቶች የሚተጫጩበት፣ አዛውንቶች ወደ ሽምግልና የሚሸጋገሩበት እሴቶችን በውስጡ የያዘ ነው።   "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው የጌዴኦ አርሶ አደር ካመረተው ምርት ለመሪው፣ ልጆች ለወላጆችና ለአሳዳጊዎቻቸው፣ አዲስ ተጋቢዎች ለአማቾቻቸው፣ ቂም የያዘ ሰው እንዲሁ የተቀየመውን ሰው ይቅርታ ለመጠየቅ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። "ጉማታ" በጌዴኦ ዘመን መለወጫ ወቅት የሚፈጸም ስጦታ ነው። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማኅበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ነው። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። በዳራሮ በዓል አከባበር ውስጥ "ጉማታ" እጅግ አስፈላጊና ትልቅ ትርጉም ያለው ባህላዊ የክብር ስጦታ የመስጠት ሥርዓት ነው። "ጉማታ" ማለት በቀጥታ ትርጉሙ "ስጦታ" ማለት ቢሆንም፣ በጌዴኦ ባህል ግን ከስጦታ በላይ ነው። ምስጋናን፣ ፍቅርን፣ አክብሮትንና በረከትን የመጋራት መገለጫ ነው።   የጌዴአ ባህላዊ የባሌ ስርዓት መሪ ሆነው የሚሰየሙት አባ ገዳ ለህዝብ ከመጸለይ፣ ከማስታረቅና ክፉን በማውገዝ ህዝቡ ተፈጥሮን እንዲንከባከብ ከማስተማር ውጭ አይዘሩም፣ አይነግዱም፣ አልፎም እንሳስትን አያረቡም፡፡ የዳራሮ በዓልን ተከትሎ ህዝቡ የሚያቀርብላቸውን "ጉማታ" በመቀበል ባህላዊ የመሪነት ሚናቸውን በአግባቡ ከመወጣት ውጪ። ኑሮው ከጥምር እርሻ ጋር የተቆራኘው የጌዴኦ ሕዝብ ዘርቶ ካጨደው፣ አርብቶ ካገኘው ከብት፣ አንቦ ከቆረጠው ማር፣ ከሁሉም በአይነት በአይነቱ ሸክፎ ዳራሮ ወደ ሚከበርበት ሶንጎ (አደባባይ) ይተማል። ለጉማታ ከሚቀርቡ ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው ስጦታዎች አንዱ ማር ነው። ማር በጌዴኦ ዘንድ የጣፋጭ ዘመንና የጤና ምልክት ተደርጎ ይወሰዳልና ዋናው ስጦታ ነው። ጌዶኦዎች ቡና፣ ቅቤና ባህላዊ ምግቦች፣ የቁም እንስሳት በግና ስንጋ እንዲሁም ገንዘብ በመያዝ በበዓሉ ውስጥ የጉማታ ስርዓት ሲደርስ ተሽቀዳድመው ለአባ ገዳው በመስጠት ምርቃት ይቀበላሉ።   "ጉማታ" የተቀበለው ሰው የሚመርቀው ምርቃት በሰጪው ሕይወት ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይታመናልና ከስጦታው ይልቅ ምርቃቱ ትልቅ ዋጋ አለው። "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው ጌዴኦ በረከትን ማካፈል ለቀጣዩ ዓመት ተጨማሪ በረከት እንደሚያገኝ ስለሚያውቅ ጉማታ መስጠት የዘመናት ቅርሱ ነው። ጉማታ ከአባ ገዳና ከባህል ሽማግሌዎች ባለፈ አርሶ አደሩ ከማጋኖ (ከፈጣሪ) ያገኘውን በረከት ለሚወዳቸውና ለሚያከብራቸው ሰዎች የሚያቀርብበት መንገድ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ገልጸዋል።   ልጆች ለወላጆቻቸውና ለቤተሰብ አባላት ላሳደጓቸውና ለሰጧቸው ምርቃት ምስጋናቸውን ለመግለጽ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። በቅርቡ ጋብቻ የመሠረቱ ወጣቶች ወደ አማቾቻቸው ቤት ጉማታ ይዞ በመሄድ ዝምድናቸውን ያጠናክራሉ። በዓመቱ ውስጥ ቅሬታ ወይም ቂም ካለ፣ በዳራሮ ወቅት ጉማታ ይዞ በመሄድ ይቅርታ ይጠየቃል። ጉማታ የሰውን ልብ ለማለስለስና አዲስ ዓመትን በሰላም ለመጀመር ያገለግላል ተብሎ ስለሚታመን። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማህበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ስለመሆኑም ነው ዋና አስተዳዳሪው የጠቆሙት። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። ይህም የመደጋገፍ እሴትን ከማጠናከር በተጓዳኝ ህዝቡ የመንግስት ገቢን እንዲሁም በማህበረሰብ ተሳትፎ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆን መሰረት የጣለ ነው ይላሉ።   የዘንድሮው ዳራሮ ከቤት በተለይም ከአባ ገዳው መኖሪያ አንስቶ በሶንጎዎችና በየደረጃው በሚገኙ መዋቅሮች በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ጭምር እየተከበረ መሆኑን ያነሱት አስተዳዳሪው ጉማታም ዋናው የበዓሉ እሴት ሆኖ እየተከበረ ነው ብለዋል። ባህልና ማንነትን በማስጠበቅና በማዳበር፣ ባህሉ ወደ ወጣቶች እንዲተላለፍ በማበረታታት እንዲሁም የጌዴኦ ባህልን ለሌሎች ህዝቦች ለማስተዋወቅና የማህበረሰብ አንድነትና ባህላዊ እሴትን ለማጠናከር እያገለገለ ያለው የጌዴኦ ዘመን መለወጫ ዳራሮ ጥር 29 እና 30 በዲላ ከተማ ይከበራል። የዳራሮ በዓል የጌዴኦን ሕዝብ የሥራ ባህል፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ዕውቀትና የሰላም እሴት ለዓለም የሚያሳይ ትልቅ አጋጣሚ ነው። ይህ በዓል በተለይ የጌዴኦ የባህላዊ መልክዓ ምድር (Cultural Landscape) በዩኔስኮ (UNESCO) በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ተከትሎ፣ አሁን ላይ ከቤትና ከአደባባይ አልፎ ዓለም አቀፋዊ ትኩረት እያገኘ ያለ ታላቅ እሴት ሆኗል። የዓመት ሰው ይበለን!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም