ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ነጌሌ አርሲ አዳማ ከተማን አሸንፏል
Apr 5, 2026 52
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡- በ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት ነጌሌ አርሲ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 ረትቷል። 9 ሠዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ፤ ሁለቱም እስከ እረፍት ድረስ ያለምንም ግብ አቻ ሆነው ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል። ከእረፍት መልስ ዳዊት ተፈራ እና ሮሆቦት ሰላሎ ለነጌሌ አርሲ እንዲሁም ዳዋ ሁቴሳ ለአዳማ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ውጤቱን ተከትሎም ነጌሌ አርሲ በ41 ነጥብ 3ኛ እንዲሁም አዳማ ከተማ በ33 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት የሚያስቀጥል የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስደናል -ወጣቶች
Apr 5, 2026 146
ጭሮ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በጠቅላላ ምርጫው የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት የሚያስቀጥል የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን በምዕራብ ሐረርጌ ዞን የሂርና ከተማ ወጣቶች ተናገሩ። የምርጫ ካርድ ያልወሰዱ ቀነ ገደቡ ሳይጠናቀቅ በመራጭነት ተመዝግበው ካርድ እንዲወስዱ ወጣቶቹ ጥሪ አቅርበዋል። የምርጫ ሂደቱን አስመልክተው የሂርና ከተማ ወጣቶች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት እንደ ሀገር የተገኙ ልማቶችን አጠናክሮ የሚያስቀጥል የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ ወስደዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ ወጣቶች መካከል ወጣት ያሲን አህመዲን እንዳለው በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት እየተሳተፈ ነው። በሀገሪቱ የተጀመሩ ሁሉን አቀፍ ልማቶችን ለማስቀጠልና ዴሞክራሲያዊ ስርአት እንዲጠናከር በሚደረገው ጥረት የበኩሉን ለማበርከት የምርጫ ካርድ መውሰዱን ተናግሯል። ሌሎችም የምርጫ ካርድ በመውሰድ የዜግነት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ መክሯል። ወጣቶች በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለዲሞክራሲ ግንባታና ለሀገር እድገት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ የጠየቀው ደግሞ ወጣት ዝያድ ያሲን ነው። ለምርጫው ፍትሀዊነትና ሰላማዊነት የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለመምረጥ የሚያስችለውን ካርድ በወቅቱ መውሰዱን ተናግሯል። የመራጭነት ካርድ ያልወሰዱ ወጣቶች የመራጮች ምዝገባ ጊዜ ሳይጠናቀቅ ተመዝግበው ካርድ እንዲወስዱ መክሯል። ሌላኛዋ የከተማው ነዋሪ ወጣት ሮዛ ያሲን በበኩሏ የበለፀገች ሀገር ለመገንባት በምርጫ በንቃት መሳተፍ ወሳኝ መሆኑን አስረድታለች። በገጠርና ከተሞች እየተስተዋለ ያለው ፈጣን ልማት ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን ገልፃ ልማቱን ለማስቀጠል ይበጃል የምትለውን ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ነው ያለችው። ለመራጮች ምዝገባ የተቀመጠው ቀነ ገደብ ሳይጠናቀቅ ህብረተሰቡ የምርጫ ካርድ እንዲውስድ ወጣቶቹ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አዲስ ስፖርት ፓርክ ለአትሌቶች የሚገባው ክብር የተሰጠበት ታሪካዊ ስራ ነው
Apr 5, 2026 108
አዲስ አበባ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ ስፖርት ፓርክ፣ ለሀገር ክብር የደከሙ ጀግኖች አትሌቶችን የሚዘክርና ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ ተነሳሽነት የሚፈጥር መሆኑን አትሌቶች ገለጹ። አዲስ ስፖርት ፓርክ ጀግኖችን ያከበረ ማዕከል ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአዲስ ስፖርት ፓርክን ትናንት መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መርቀው ለህዝብ ክፍት አደርገዋል። በዚሁ ወቅትም የአዲስ ስፖርት ፓርክ የመዲናዋን ዕድሳት በማፋጠን የዜጎችን ክብር ለመመለስ የተገባው ቃል መተግበሩን አንዱ ማረጋገጫ እንደሆነ ገልጸዋል። በአምስት ነጥብ ሰባት ሄክታር መሬት ላይ ባረፈው ፓርክም በዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ መድረክ ኢትዮጵያን ክብር ያጎናጸፉ 15 ጀግና አትሌቶች ሐውልት ቆሞላቸዋል። ለተተኪ ትወልድ በትዕምርትነት የሚያገለግለው ፓርክ ዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ ደረጃን ያሟሉ ዘመናዊ የመዋኛ ገንዳ፣ የእግርና የቅርጫት ኳስ፣ የቴኒስና የሩጫ ትራክና ሜዳዎችን የያዘ ማዕከል ነው። በአዲስ ስፖርት ፓርክ ሐውልት የቆመላቸውና በምርቃቱ ላይ የታደሙ አንጋፋና ወጣት አትሌቶች ፓርኩ መገንባቱ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረላቸው ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል። አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በሰጠው አስተያየት፤ ቀደም ሲል በውጭ ሀገራት የሚያዩዋቸውን መሰል ዘመናዊ ስፍራዎች ሀገር ውስጥ ተገንብቶ በማየቱ ታላቅ ደስታ ተሰምቶኛል ብሏል። አዲስ አበባን ሳቢ በማድረግ በምሽት ጭምር አገልግሎት የሚሰጡ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጿል። በዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ መድረክ የሀገራቸውን ክብር ከፍ ላደረጉ ጀግና አትሌቶች የመታሰቢያ ሐውልት መቆሙም ከፍተኛ ኩራት እንደተሰማው በመግለፅ፤ ለዚህም ምስጋና አቅርቧል። አትሌት ገዛኸኝ አበራ እንደገለጸው፤ በእነርሱ ዘመን ያልነበሩ ዘመናዊ የሩጫ ትራኮች አሁን ላይ በስፋት መገንባታቸው የተተኪ ስፖርተኞችን ችግር ያቃልላል። መንግሥት ለአትሌቶች በሰጠው ክብር አመስግኖ፣ ኢትዮጵያ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ የሚያስችሏት የመሠረተ ልማት ሥራዎች መከናወናቸው የሚደነቅ መሆኑን ተናግሯል። ኢትዮጵያ በሰራቻቸው የስፖርት ፓርክና የኮሪደር ልማት በሌሎች አገራት አድናቆት እያገኘች መምጣቷንም ገልጿል። "በህይወት እያለሁ ታሪኬን የሚዘክር ሐውልት በመቆሙ ዳግም እንደተወለድኩ ሆኖ ተሰምቶኛል" ያለው ኮማንደር አትሌት ታምራት ቶላ፤ ለመንግስት ምስጋናውን አቅርቧል። አሁን ላይ በስፋት የተገነቡ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የመሮጫ ትራኮችን ወጣቱ በአግባቡ በመጠቀም የሀገሩን ስም እንዲያስጠራ አትሌቱ ጥሪ አቅርቧል። ኮማንደር አትሌት ሰለሞን ባረጋም በኦሎምፒክ መድረኮች ብቻ የሚታዩ ጥራት ያላቸው ስራዎች በሀገሩ በመገንባታቸው የተሰማውን ኩራት ገልጿል። ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ያላትን ፀጋ አልምቶ ለመጠቀም መንግስት የጀመረው ስራ ታላቅ ተምሳሌት መሆኑን አትሌቶቹ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን በበኩሉ፤ መንግስት ለስፖርት ማዘውተሪያዎች የሰጠው ትኩረት ለዘርፉ ዕድገት አዲስ ዕድል መፍጠሩን ገልጿል። እንደ አደይ አበባ ስታዲየም እና አዲስ ስፖርት ፓርክ ያሉ ግዙፍ ግንባታዎች ኢትዮጵያ የዓለም ሻምፒዮናዎችን በልበ ሙሉነት እንድታስተናግድ የሚያስችሏት መሆኑንም ጠቁሟል። ይህ በምሽትም ጭምር የሚያገለግለው ዘመናዊ መሰረተ ልማት አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ይበልጥ ተስማሚና ሳቢ ከማድረጉም በላይ ለስፖርቱ እድገት አዲስ ተስፋ የፈነጠቀ መሆኑንም ተናግሯል።
አዲስ ስፖርት ፓርክ ጀግኖችን ያከበረ ማዕከል ነው
Apr 5, 2026 164
አዲስ አበባ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በአዲስ አበባ ዑራኤል አካባቢ የተገነባው የአዲስ ስፖርት ፓርክ የስፖርቱን ዘርፍ የዘመናት መሻት እውን ያደረገ ድንቅ የሥራ ውጤት ሆኗል። አዲስ ስፖርት ፓርክ ለአትሌቶች የሚገባው ክብር የተሰጠበት ታሪካዊ ስራ ነው የአዲስ ስፖርት ፓርክም ስሙ ብቻ ሳይሆን ይዘቱም አዲስ ነው። ኢትዮጵያ ለጀግኖቿ ያላትን ክብር የገለጸችበት፣ለተተኪዎቿም የተስፋ ብርሃን የለኮሰችበት የስፖርት አውድ ለመሆን በቅቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትናንት መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መርቀው የከፈቱት ይህ ፓርክ፣ የመወዳደሪያ ስፍራ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ሁሉን አቀፍ ልማት ጉዞ እንደሚያሳይ ተገልጿል። በፓርኩም የስፖርት መሠረተ ልማት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አደባባይ በአንጸባራቂ ድሎቻቸው ያውለበለቡ ድንቅ የአትሌቲክስ ፈርጦች ሐውልት ቆሟል። በዚህ ታሪካዊ ስፍራ ሐውልት ከቆመላቸው 15 የኢትዮጵያ እንቁ አትሌቶች መካከል ስድስቱ እንስት ጀግና አትሌቶች ሃሳባቸውን አጋርተውናል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፈር ቀዳጇ አትሌት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፤ ፓርኩን ስትመለከት የታያት የሀገር ከፍታ ነው። "እንዲህ ዓይነት ፓርክ በውጭ ሀገር ስንመለከት እንመኘው ነበር፤ ዛሬ በሀገራችን ተሰርቶ ማየቴ ታላቅ ደስታ ነው" ትላለች። አትሌት ደራርቱ አክላም፣ ፓርኩ የኢትዮጵያን የኦሎምፒክ ተሳትፎ እንደሚለውጥ ገልጻ፤ "እኛ በባዶ እግር ነው የጀመርነው፤ አሁን ግን መሰረተ ልማት ተሟልቶ በፕሮፌሽናል ደረጃ መሰልጠን ተችሏል።እንዲህ ያሉ ስራዎች ከተጠናከሩ 15 ሳይሆን 15 ሺህ ወርቅ እናመጣለን" ስትል ለወደፊቱ ትውልድ ያላትን ትልቅ ተስፋ አጋርታለች። የማራቶን ድል አድራጊዋ አትሌት ኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ በፓርኩ ውስጥ የቆመው ሐውልት ትርጉም በቃላት የማይገለጽ መሆኑን ትናገራለች። "ሐውልታችን መቆሙ ለእኛም ሞራል ለሚቀጥለው ትውልድም ትምህርት ነው" የምትለው ፋጡማ፣ይህ ስፍራ ለልጅ ልጅ የሚተርፍ የስኬት ማስታወሻ መሆኑን ገልጻለች። በውጭ ሀገራት የምናያቸው ጥራት ያላቸው የስፖርት ፓርኮች ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር ላይ መገንባታቸው ለስፖርቱ እድገት አቅም እንደሚሆንም አብራርታለች። የረጅም ርቀት ንግሥቷ ኮማንደር ጥሩነሽ ዲባባ፣የሐውልቱን መቆም ከሀገር ክብርና ከትውልድ ቅብብሎሽ ጋር አስተሳስራዋለች። ድሮ እኛ በነባር አትሌቶች ተነሳስተን ነው እዚህ የደረስነው የምትለው ደማቋ አትሌት፥ ዛሬ ደግሞ ተተኪዎች የእኛን ሐውልት ሲያዩ ለታላቅነት መነሳሳት ይፈጥርላቸዋል ትላለች። ጀግኖችን በሕይወት እያሉ ማክበር ለሚመጣው ትውልድ ለሀገሩ ትልቅ ሥራ እንዲሠራ መነሳሳት የሚፈጥርና ምሳሌ እንደሚሆንም በኩራት ገልጻለች። ለአትሌት መሰረት ደፋር አዲስ ስፖርት ፓርክ ማመን እስኪያቅታት ነው የሆነባት። "ቃላት ያጥረኛል" የምትለው አትሌቷ፤ ኡራኤል አካባቢን በዚህ ገጽታ አየዋለሁ ብዬ አላመንኩም በማለት ነበር ስሜቷን የገለጸችው። አትሌት መሰረት ቀደም ሲል በአዲስ አበባ መሮጫ ስፍራ እንኳን እንዳልነበረ አስታውሳ፤ አሁን ግን ህዝቡ ጤናውን የሚጠብቅበት ውብ ቦታ መዘጋጀቱን ታደንቃለች። አልባሌ ቦታ ከመዋል እዚህ መጥቶ ሀገርን ለማስጠራት መስራት ይገባል በማለትም ለወጣቶች ጥሪዋን አስተላልፋለች። አትሌት ሃምሳ አለቃ አልማዝ አያና በበኩሏ የፓርኩን ጥራትና ምሉዕነት አድንቃለች። "ምንም እንከን የሚወጣለት ነገር የለም፤ ይህ ልዩ ነው" የምትለው አትሌት አልማዝ፣ፓርኩ ስፖርት አቁመው የነበሩትን እንኳን ዳግም ወደ ሜዳ እንዲመለሱ የሚያደርግ እንደሆነ ትገልጻለች። በመንግሥት ለስፖርት ዘርፉ የተሰጠ ትልቅ ሥፍራ መሆኑንም ትመሰክራለች። አትሌት መቶ አለቃ ቲኪ ገላና ፓርኩ ሁሉንም ስፖርት በአንድ ማዕከል መያዙ ልዩ ያደርገዋል ብላለች። ለሀገር አቋራጭ መሮጫ የሚሆን ስፍራ፣ የዋና፣ የእግር ኳስና ሌሎች ስፖርቶችን መሠረተ ልማት ማካተቱ ለኢትዮጵያ ስፖርት ከፍታ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ጠቁማለች። አትሌቶቹ አዲስ ስፖርት ፓርክ የኢትዮጵያን የነገ ተስፋ በፅኑ መሰረት ላይ የጣለ ታላቅ ስራ መሆኑን ገልጸዋል።
ለምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊነት የበኩላችንን ሚና እንወጣለን
Apr 5, 2026 180
አዲስ አበባ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊነት የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉ ወጣቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል፤ የመራጮች ምዝገባም እየተከናወነ ይገኛል። በምርጫው ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶች በምርጫ ታዛቢነት እንደሚሳተፉ ተመላክቷል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ዓለም አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አሌክሳንደር ንጉሥ ከኢዜአ ጋር ባደረገው ቆይታ እንደገለጸው፤ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና አካታች እንዲሆን ፌዴሬሽኑ የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም መሠረት ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡና በፌዴሬሽኑ ሥር የሚገኙ ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶች በታዛቢነት ተመዝግበው ለሥራ መዘጋጀታቸውን አረጋግጧል። ምርጫ ለአገር ዕድገትና ለዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማይተካ ሚና እንዳለው የገለጸው ወጣት አሌክሳንደር፤ ወጣቶችን በሀገሪቷ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለመጻኢ ዕድላቸው መሠረት ሊጥሉ ይገባል ነው ያለው። በተለይም የሥልጣን ሽግግር በምርጫና በምርጫ ብቻ ሊሆን እንደሚገባ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እንደተከናወነም ነው የገለጸው። የነገዋን ኢትዮጵያ የመረከብ ኃላፊነት ያለባቸው ወጣቶች፣ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው በምርጫው ወቅት የሚጠበቅባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት እንዲወጡም ጥሪ አቅርቧል። ወጣቶች የነገዋን ኢትዮጵያ መገንባትና ማስቀጠል ላይ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልፆ፤ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በምርጫ በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ ተናግሯል። በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች በበኩላቸው፣ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ወጣት ሩት ሸዋንቅጣው እንደምትናገረው፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ዲሞክራሲያዊ መብቷን ለመጠቀም ተዘጋጅታለች። በምርጫው ከመሳተፍ ባለፈ የሌሎችን ግንዛቤ ለማሳደግ እንደምትሰራ የገለፀችው ደግሞ ወጣት ቢታንያ አለምሰገድ ነች። ወጣት ናታኔም ፀጋ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑ ወጣቶች በንቃት ልንሳተፍ ይገባል ብላለች። የምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም ወጣቶቹ አረጋግጠዋል፡፡
ፖለቲካ
የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት የሚያስቀጥል የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስደናል -ወጣቶች
Apr 5, 2026 146
ጭሮ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በጠቅላላ ምርጫው የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት የሚያስቀጥል የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን በምዕራብ ሐረርጌ ዞን የሂርና ከተማ ወጣቶች ተናገሩ። የምርጫ ካርድ ያልወሰዱ ቀነ ገደቡ ሳይጠናቀቅ በመራጭነት ተመዝግበው ካርድ እንዲወስዱ ወጣቶቹ ጥሪ አቅርበዋል። የምርጫ ሂደቱን አስመልክተው የሂርና ከተማ ወጣቶች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት እንደ ሀገር የተገኙ ልማቶችን አጠናክሮ የሚያስቀጥል የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ ወስደዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ ወጣቶች መካከል ወጣት ያሲን አህመዲን እንዳለው በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት እየተሳተፈ ነው። በሀገሪቱ የተጀመሩ ሁሉን አቀፍ ልማቶችን ለማስቀጠልና ዴሞክራሲያዊ ስርአት እንዲጠናከር በሚደረገው ጥረት የበኩሉን ለማበርከት የምርጫ ካርድ መውሰዱን ተናግሯል። ሌሎችም የምርጫ ካርድ በመውሰድ የዜግነት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ መክሯል። ወጣቶች በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለዲሞክራሲ ግንባታና ለሀገር እድገት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ የጠየቀው ደግሞ ወጣት ዝያድ ያሲን ነው። ለምርጫው ፍትሀዊነትና ሰላማዊነት የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለመምረጥ የሚያስችለውን ካርድ በወቅቱ መውሰዱን ተናግሯል። የመራጭነት ካርድ ያልወሰዱ ወጣቶች የመራጮች ምዝገባ ጊዜ ሳይጠናቀቅ ተመዝግበው ካርድ እንዲወስዱ መክሯል። ሌላኛዋ የከተማው ነዋሪ ወጣት ሮዛ ያሲን በበኩሏ የበለፀገች ሀገር ለመገንባት በምርጫ በንቃት መሳተፍ ወሳኝ መሆኑን አስረድታለች። በገጠርና ከተሞች እየተስተዋለ ያለው ፈጣን ልማት ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን ገልፃ ልማቱን ለማስቀጠል ይበጃል የምትለውን ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ነው ያለችው። ለመራጮች ምዝገባ የተቀመጠው ቀነ ገደብ ሳይጠናቀቅ ህብረተሰቡ የምርጫ ካርድ እንዲውስድ ወጣቶቹ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ለምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊነት የበኩላችንን ሚና እንወጣለን
Apr 5, 2026 180
አዲስ አበባ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊነት የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉ ወጣቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል፤ የመራጮች ምዝገባም እየተከናወነ ይገኛል። በምርጫው ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶች በምርጫ ታዛቢነት እንደሚሳተፉ ተመላክቷል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ዓለም አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አሌክሳንደር ንጉሥ ከኢዜአ ጋር ባደረገው ቆይታ እንደገለጸው፤ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና አካታች እንዲሆን ፌዴሬሽኑ የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም መሠረት ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡና በፌዴሬሽኑ ሥር የሚገኙ ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶች በታዛቢነት ተመዝግበው ለሥራ መዘጋጀታቸውን አረጋግጧል። ምርጫ ለአገር ዕድገትና ለዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማይተካ ሚና እንዳለው የገለጸው ወጣት አሌክሳንደር፤ ወጣቶችን በሀገሪቷ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለመጻኢ ዕድላቸው መሠረት ሊጥሉ ይገባል ነው ያለው። በተለይም የሥልጣን ሽግግር በምርጫና በምርጫ ብቻ ሊሆን እንደሚገባ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እንደተከናወነም ነው የገለጸው። የነገዋን ኢትዮጵያ የመረከብ ኃላፊነት ያለባቸው ወጣቶች፣ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው በምርጫው ወቅት የሚጠበቅባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት እንዲወጡም ጥሪ አቅርቧል። ወጣቶች የነገዋን ኢትዮጵያ መገንባትና ማስቀጠል ላይ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልፆ፤ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በምርጫ በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ ተናግሯል። በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች በበኩላቸው፣ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ወጣት ሩት ሸዋንቅጣው እንደምትናገረው፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ዲሞክራሲያዊ መብቷን ለመጠቀም ተዘጋጅታለች። በምርጫው ከመሳተፍ ባለፈ የሌሎችን ግንዛቤ ለማሳደግ እንደምትሰራ የገለፀችው ደግሞ ወጣት ቢታንያ አለምሰገድ ነች። ወጣት ናታኔም ፀጋ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑ ወጣቶች በንቃት ልንሳተፍ ይገባል ብላለች። የምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም ወጣቶቹ አረጋግጠዋል፡፡
ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ዕድገት የተሻለ የፖሊሲ አማራጭ ያቀረበን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስደናል - ነዋሪዎች
Apr 5, 2026 152
ድሬደዋ ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ዕድገት የተሻለ የፖሊሲ አማራጭ ያቀረበን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የድሬዳዋ ነዋሪዎች ገለጹ። ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በድሬዳዋ አስተዳደር በተዘጋጁት የምርጫ ጣቢያዎች ነዋሪዎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በአካልና በዲጂታል አገልግሎት እያወጡ ይገኛሉ። ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት ዕድሜያቸው ለመራጭነት የደረሱ ዜጎች የምርጫ ካርዳቸውን በመውሰድ ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መክረዋል። ነዋሪዎቹ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ዕድገት የሚበጅ አማራጭ ፖሊሲ ያቀረበን የፖለቲካ ፓርቲን ለመምረጥ ካርድ አውጥተዋል። አቶ ገዛኸኝ ተክሌ፤ ምርጫ ለሀገር ዴሞክራሲያዊ ስርአት መዳበር እና ለመድበለ ፓርቲ ስርአት መጠናከር አበርክቶው የጎላ እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸዋል። ለዚህም የመምረጥ ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ማውጣታቸውን ተናግረዋል ። ወይዘሮ ትዕግስት መዝገቡ በበኩላቸው፤ የምርጫ ካርዳቸውን በማውጣት የመምረጥ መብታቸውን ለማረጋገጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረው ሌሎችም የዜግነት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ከልምዳቸው መክረዋል። እሳቸውም በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ተአማኒ ምርጫ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሚናቸውን እንደሚወጡም አክለዋል ። አቶ ወንደውሰን ደምሴ በበኩላቸው፤ በዘንድሮ 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እያቀረቡ የሚገኙትን የክርክር ሃሳቦች በመገናኛ ብዙሃን እየተከታተሉ መሆኑን ተናግረዋል። እየተካሄዱ የሚገኙት ክርክሮች የዜጎችን የምርጫ ተሳትፎ እያሳደጉ መሆናቸውንም አንስተዋል። ወጣት ኦብሳ አደም የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ወጣቶች የድርሻቸውን መወጣት አለባቸው ብሏል። እሱም ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ መውሰዱን ጠቅሶ በመጪው ግንቦት በሚካሄደው ምርጫ ለድሬዳዋ ብሎም ለሀገር ዕድገት ይሰራል የሚለውን ፓርቲ እንደሚመረጥ ገልጿል ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃግብር መሠረት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ ተገልጿል።
የመጋቢት 24ቱ ለውጥ ሀገሪቷን ከተደቀኑባት ትላልቅ ስጋቶች ያተረፈ ነው
Apr 5, 2026 337
ጅግጅጋ፣መጋቢት 27/2018(ኢዜአ)፦የመጋቢት 24ቱ ለውጥ ሀገሪቷን ተደቅነውባት ከነበረ ውስጣዊና ውጫዊ ስጋቶች ያተረፈ ነው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር መሀመድ ሻሌ ገለጹ። የመጋቢት 24ቱ ሀገራዊ ለውጥ 8ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር መሀመድ ሻሌ በህዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ ላይ እንደገለጹት፣ የመጋቢት 24ቱ ለውጥ የክልሉ ሠላምና ልማት የተጠናከረበት እና ህብረ ብሔራዊ አንድነት የጎለበተበት ነው። በተለይም የሶማሌ ክልል ቀደም ሲል ከነበረበት የሠላምና ልማት ችግር ወጥቶ በሀገሪቱ ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎን ያረጋገጠበት ነው ብለዋል። እለቱ ኢትዮጵያን ተደቅነውባት ከነበረው ውጫዊና ውስጣዊ ስጋቶች ያተረፈ መሆኑን ገልጸው፤ መጋቢት 24 ክልሉም በሀገሪቷ ፖለቲካዊ እኩል ተሳትፎ ያሳደገበት መሆኑን ነው ያነሱት። በለውጡ አመታት በሀገሪቷ ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች የተጀመረበት እና የተጠናቀቀበት መሆኑንም ገልጸዋል። የጅግጅጋ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ሻፊ አህመድ በበኩላቸው፥ የመጋቢት 24 ለውጥ የዜጎች የሠላም፣የልማትና የመልካም አስተዳደር ተሳትፎ የተቀየረበትና የህዝቡን ችግሮች የፈቱ የልማት ሥራዎች የተከናወኑበት ነው ብለዋል። ከለውጡ በፊት ክልሉ የሠላም ፤ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ችግሮች የነበረበት እንደነበረ አንስተው፤ከለውጡ በኋላ ወደ ልማት በመግባት የብልጽግና ተምሳሌት ሆኗል ብለዋል። የክልሉ ህዝብ ከስጋትና ፍርሃት የወጣበትና የሀገሪቷ የፖለቲካ ተሳትፎ የጨመረበት መሆኑንም አክለዋል። ጅግጅጋ ከተማ የከተሞች ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን በመጥቀስ በሀገራዊ ለወጡ የተገኘው ሠላም እና ልማትን ለማስቀጠል ህዝቡ ተሳትፎውን እንዲያስቀጥልም አሳስበዋል። በድጋፍ ሰልፉ ላይ መጋቢት 24 ታሪካዊ ቀን የሚታወስበት ነው፤ የድልም ትሩፋት የተገኘበትና ሠላማችን የተረጋገጠበት ቀን ነው የሚሉና ሌሎች መልዕክቶች ተላልፈዋል።
ይበጀናል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል - መራጮች
Apr 5, 2026 312
ጎንደር ፤ መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገር ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን አስተያየታቸውን የሰጡ የጎንደር ከተማ መራጮች ተናገሩ፡፡ የዲላ ከተማ ነዋሪዎች በጠቅላላ ምርጫው ድምፅ ለመስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ነው የጎንደር ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ገበያው ተረፈ ለኢዜአ እንደገለጹት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በምርጫ ተወዳድሮ የተመረጠ መንግስት ለሀገር እድገትና ብልጽግና መሰረት ነው። ይህን በመገንዘባቸውም ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ቀድመው በማውጣት የምርጫውን እለት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አስረድተዋል። የከተማዋ ነዋሪ ወጣት ፋሲል ጀመረ በበኩሉ ምርጫ የሀገራችንን የወደፊት እጣ ፈንታ የምንወስንበት መሆኑን ሁሉም ሰው ሊገነዘብ ይገባል ሲል ገልጿል። በዚህም ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው መምረጥ እንዲችሉ የምርጫ ካርድ ጊዜው ከማብቃቱ በፊት ማውጣት አለባቸው ብሏል። ምርጫ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ መሪውን ለስልጣን የሚያበቃበት በመሆኑ እኔም ባወጣሁት ካርድ የምፈልገውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ሲል ተናግሯል፡፡ ወይዘሮ ወርቄ ታደሰም ለሴቶች እኩልነት፣ መብትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የቆመ ፓርቲን ለመምረጥ የሚያስችለኝን የምርጫ ካርድ አውጥቻለሁ ብለዋል። ካርዴንም ለህዝቡ ኑሮ መለወጥ እንዲሁም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጥ እጠቀምበታለሁ ሲሉ ገልጸዋል። በሚዲያ እየተካሄደ ያለው ክርክር ፓርቲዎች ያላቸውን ፖሊሲና ፕሮግራም ለመገንዘብ እያስቻላቸው በመሆኑ በምርጫው እለት ድምጽ ለመስጠት እንደማይቸገሩ አስተያየት ሰጪዎች አረጋግጠዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገው የጊዜ ሰሌዳ ያመለክታል፡፡
የዲላ ከተማ ነዋሪዎች በጠቅላላ ምርጫው ድምፅ ለመስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ነው
Apr 5, 2026 251
ዲላ ፤ መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ መሆኑን የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ለዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን እያስተዋወቁ ሲሆን መራጮችም የምርጫ ካርዳቸውን በመውሰድ ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ የበኩላቸውን ለማበርከትና ዜግነት ሀላፊነታቸውን ለመወጣት እየሰሩ ናቸው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዲላ ከተማ ነዋሪዎች፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ በመስጠት ህገ-መንግሥታዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ እሸቱ ፀጋዬ በምርጫው በንቃት መሳተፍ የዜግነት ግዴታቸው መሆኑን አንስተዋል። የምርጫ ዴሞክራሲያዊነት የሚወሰነው በዜጎች ተሳትፎ ልክ በመሆኑ ለዚህም የምርጫ ካርድ በመውሰድ የድርሻቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። ይህም በቀጣይ አምስት ዓመታት በአግባቡ ይመረኛል፣ ይጠቅመኛል ብለው ያመኑበትን ፓርቲ ለመምረጥ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል። በምርጫው ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም ካርድ መውሰዳቸውን ያነሱት ደግሞ ወይዘሮ እመቤት ደበሌ ናቸው። ምርጫ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መንግስት የሚሰየምበት መሆኑን አንስተው ለዚህም የመራጭነት ካርድ በመውሰድ መምረጥ እንደሚገባም አንስተዋል። ሌላኛው የከተማው ነዋሪ ያውቃል ሞላ በበኩላቸው፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ይህም የፈለገውን እና ያመነበትን ፓርቲ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም እንደሚያስችላቸው ነው የጠቀሱት። ምርጫው ሠላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ድምፅ በመስጠት ህገ-መንግሥታዊ መብቱን ለመጠቀም መዘጋጀቱን ያነሳው ደግሞ ወጣት ልኡል በቀለ ነው። በምርጫው የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ የምርጫ ካርድ መያዝ ወሳኝ በመሆኑ የመራጭነት ካርድ መውሰዱን ተናግሮ ሌሎችም በቀሩት ቀናት ካርድ እንዲወስዱ ጠቁሟል።
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 14 ተራዘመ
Apr 4, 2026 1296
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሲያከናውን የቆየውን የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን አስታወቀ። ቦርዱ ቀደም ሲል ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲከናወን መታቀዱን አስታውሷል። የምዝገባ ሂደቱን በቴክኖሎጂ ለማገዝ በወጣው ዕቅድ መሠረትም የዕጩዎች ምዝገባ በአሁኑ ወቅት መጠናቀቁንና የመራጮች ምዝገባ ደግሞ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ሲከናወን መቆየቱን ገልጿል። ሆኖም በምዝገባ ሂደቱ ወቅት በተወሰኑ አካባቢዎች በቴክኖሎጂ የታገዘውን አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ የኔትወርክ አቅርቦት ችግር ማጋጠሙን ቦርዱ ገልጿል። ይህንን ተግዳሮት በመቅረፍ ሂደቱን አስተማማኝና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጠቀመውን ተጨማሪ ጊዜ ለማካካስ የምዝገባውን ጊዜ ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብሏል። በተጨማሪም አስተማማኝ የኔትወርክ አቅርቦት ይኖራቸዋል ተብለው በታሰቡ አንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የኔትወርክ መቋረጥ በማጋጠሙ፣ ሂደቱን ወደ ማኑዋል (በእጅ) አሠራር በመቀየር ረገድ የባከነውን ጊዜ ለመተካት መወሰኑን በመግለጫው አመልክቷል። በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች በነበረ የትራንስፖርት ችግር ምክንያት የምዝገባ ቁሳቁሶች በወቅቱ ባለመድረሳቸው ለተፈጠረው መዘግየት ምላሽ ለመስጠት፣ ቦርዱ የመራጮች ምዝገባው ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም ማድረጉን አስታውቋል።
መጋቢት 24 የሶማሌ ክልል ህዝብ ትክክለኛ ውክልና ያገኘበትና አዲስ የፖለቲካ ባህል የታየበት ዕለት ነው
Apr 4, 2026 721
ጅግጅጋ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ መጋቢት 24 የሶማሌ ክልል ህዝብ ትክክለኛ ውክልና ያገኘበትና አዲስ የፖለቲካ ባህል የታየበት ዕለት ነው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ገለጸ። የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ኢንጂነር መሀመድ ሻሌ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ መጋቢት 24 የሶማሌ ክልል ህዝብ ትክክለኛ ውክልና ያገኘበትና አዲስ የፖለቲካ ልምምድ የጀመረበት ዕለት ነው ብለዋል። ከለውጡ የሶማሌ ክልል የሠላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ችግሮች የነበሩበት መሆኑን አስታውሰው ከለውጡ ወዲህ ለችግሮቹ መፍትሄ በመገኘቱ በክልሉ አሁን ላይ ውጤታማ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። በለውጡ ዓመታት በተከናወኑ ሪፎርሞች በክልሉ ሁለንተናዊ ልማት እየተረጋገጠ መሆኑን ገልፀው ከአግላይና ከፋፋይ የፖለቲካ ሥርዓት በመውጣት አዲስ የፖለቲካ ባህል መታየቱንም አክለዋል። በአሁኑ ወቅት መንግስትና ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር በመስራት ላይ እንደሚገኙ አንስተው በክልሉ በተፈጠረው ምቹ የፖለቲካ ምህዳር በጠቅላላ ምርጫው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚወዳደሩም ገልጸዋል። በጸጥታና በፍትህ ተቋማት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውንና የማጠናከር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በክልሉ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸውን በመጥቀስ በቀጣይም በክልሉ የሚገኙ ፀጋዎችን በተገቢው መንገድ መጠቀም የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። በክልሉ ተግባራዊ የተደረጉ አዳዲስ ኢኒሼቲቮች ዘርፈ ብዙ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸው ህብረተሰቡን በሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራት ይጠናከራሉ ብለዋል። ክልሉን የቱሪዝም የስበት ማዕከል ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች በውጤታማነት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ማህበረሰቡን ከተረጂነት ለማውጣት የተጀመሩ የግብርና ልማት ሥራዎች የበለጠ እንደሚጠናከሩም አረጋግጠዋል።
ፖለቲካ
የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት የሚያስቀጥል የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስደናል -ወጣቶች
Apr 5, 2026 146
ጭሮ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በጠቅላላ ምርጫው የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት የሚያስቀጥል የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን በምዕራብ ሐረርጌ ዞን የሂርና ከተማ ወጣቶች ተናገሩ። የምርጫ ካርድ ያልወሰዱ ቀነ ገደቡ ሳይጠናቀቅ በመራጭነት ተመዝግበው ካርድ እንዲወስዱ ወጣቶቹ ጥሪ አቅርበዋል። የምርጫ ሂደቱን አስመልክተው የሂርና ከተማ ወጣቶች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት እንደ ሀገር የተገኙ ልማቶችን አጠናክሮ የሚያስቀጥል የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ ወስደዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ ወጣቶች መካከል ወጣት ያሲን አህመዲን እንዳለው በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት እየተሳተፈ ነው። በሀገሪቱ የተጀመሩ ሁሉን አቀፍ ልማቶችን ለማስቀጠልና ዴሞክራሲያዊ ስርአት እንዲጠናከር በሚደረገው ጥረት የበኩሉን ለማበርከት የምርጫ ካርድ መውሰዱን ተናግሯል። ሌሎችም የምርጫ ካርድ በመውሰድ የዜግነት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ መክሯል። ወጣቶች በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለዲሞክራሲ ግንባታና ለሀገር እድገት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ የጠየቀው ደግሞ ወጣት ዝያድ ያሲን ነው። ለምርጫው ፍትሀዊነትና ሰላማዊነት የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለመምረጥ የሚያስችለውን ካርድ በወቅቱ መውሰዱን ተናግሯል። የመራጭነት ካርድ ያልወሰዱ ወጣቶች የመራጮች ምዝገባ ጊዜ ሳይጠናቀቅ ተመዝግበው ካርድ እንዲወስዱ መክሯል። ሌላኛዋ የከተማው ነዋሪ ወጣት ሮዛ ያሲን በበኩሏ የበለፀገች ሀገር ለመገንባት በምርጫ በንቃት መሳተፍ ወሳኝ መሆኑን አስረድታለች። በገጠርና ከተሞች እየተስተዋለ ያለው ፈጣን ልማት ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን ገልፃ ልማቱን ለማስቀጠል ይበጃል የምትለውን ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ነው ያለችው። ለመራጮች ምዝገባ የተቀመጠው ቀነ ገደብ ሳይጠናቀቅ ህብረተሰቡ የምርጫ ካርድ እንዲውስድ ወጣቶቹ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ለምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊነት የበኩላችንን ሚና እንወጣለን
Apr 5, 2026 180
አዲስ አበባ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊነት የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉ ወጣቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል፤ የመራጮች ምዝገባም እየተከናወነ ይገኛል። በምርጫው ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶች በምርጫ ታዛቢነት እንደሚሳተፉ ተመላክቷል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ዓለም አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አሌክሳንደር ንጉሥ ከኢዜአ ጋር ባደረገው ቆይታ እንደገለጸው፤ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና አካታች እንዲሆን ፌዴሬሽኑ የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም መሠረት ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡና በፌዴሬሽኑ ሥር የሚገኙ ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶች በታዛቢነት ተመዝግበው ለሥራ መዘጋጀታቸውን አረጋግጧል። ምርጫ ለአገር ዕድገትና ለዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የማይተካ ሚና እንዳለው የገለጸው ወጣት አሌክሳንደር፤ ወጣቶችን በሀገሪቷ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለመጻኢ ዕድላቸው መሠረት ሊጥሉ ይገባል ነው ያለው። በተለይም የሥልጣን ሽግግር በምርጫና በምርጫ ብቻ ሊሆን እንደሚገባ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እንደተከናወነም ነው የገለጸው። የነገዋን ኢትዮጵያ የመረከብ ኃላፊነት ያለባቸው ወጣቶች፣ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው በምርጫው ወቅት የሚጠበቅባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት እንዲወጡም ጥሪ አቅርቧል። ወጣቶች የነገዋን ኢትዮጵያ መገንባትና ማስቀጠል ላይ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልፆ፤ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በምርጫ በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ ተናግሯል። በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች በበኩላቸው፣ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ወጣት ሩት ሸዋንቅጣው እንደምትናገረው፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ዲሞክራሲያዊ መብቷን ለመጠቀም ተዘጋጅታለች። በምርጫው ከመሳተፍ ባለፈ የሌሎችን ግንዛቤ ለማሳደግ እንደምትሰራ የገለፀችው ደግሞ ወጣት ቢታንያ አለምሰገድ ነች። ወጣት ናታኔም ፀጋ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑ ወጣቶች በንቃት ልንሳተፍ ይገባል ብላለች። የምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም ወጣቶቹ አረጋግጠዋል፡፡
ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ዕድገት የተሻለ የፖሊሲ አማራጭ ያቀረበን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስደናል - ነዋሪዎች
Apr 5, 2026 152
ድሬደዋ ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦ ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ዕድገት የተሻለ የፖሊሲ አማራጭ ያቀረበን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የድሬዳዋ ነዋሪዎች ገለጹ። ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በድሬዳዋ አስተዳደር በተዘጋጁት የምርጫ ጣቢያዎች ነዋሪዎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በአካልና በዲጂታል አገልግሎት እያወጡ ይገኛሉ። ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት ዕድሜያቸው ለመራጭነት የደረሱ ዜጎች የምርጫ ካርዳቸውን በመውሰድ ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መክረዋል። ነዋሪዎቹ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ዕድገት የሚበጅ አማራጭ ፖሊሲ ያቀረበን የፖለቲካ ፓርቲን ለመምረጥ ካርድ አውጥተዋል። አቶ ገዛኸኝ ተክሌ፤ ምርጫ ለሀገር ዴሞክራሲያዊ ስርአት መዳበር እና ለመድበለ ፓርቲ ስርአት መጠናከር አበርክቶው የጎላ እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸዋል። ለዚህም የመምረጥ ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ማውጣታቸውን ተናግረዋል ። ወይዘሮ ትዕግስት መዝገቡ በበኩላቸው፤ የምርጫ ካርዳቸውን በማውጣት የመምረጥ መብታቸውን ለማረጋገጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረው ሌሎችም የዜግነት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ከልምዳቸው መክረዋል። እሳቸውም በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ተአማኒ ምርጫ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሚናቸውን እንደሚወጡም አክለዋል ። አቶ ወንደውሰን ደምሴ በበኩላቸው፤ በዘንድሮ 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እያቀረቡ የሚገኙትን የክርክር ሃሳቦች በመገናኛ ብዙሃን እየተከታተሉ መሆኑን ተናግረዋል። እየተካሄዱ የሚገኙት ክርክሮች የዜጎችን የምርጫ ተሳትፎ እያሳደጉ መሆናቸውንም አንስተዋል። ወጣት ኦብሳ አደም የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ወጣቶች የድርሻቸውን መወጣት አለባቸው ብሏል። እሱም ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ መውሰዱን ጠቅሶ በመጪው ግንቦት በሚካሄደው ምርጫ ለድሬዳዋ ብሎም ለሀገር ዕድገት ይሰራል የሚለውን ፓርቲ እንደሚመረጥ ገልጿል ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃግብር መሠረት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ ተገልጿል።
የመጋቢት 24ቱ ለውጥ ሀገሪቷን ከተደቀኑባት ትላልቅ ስጋቶች ያተረፈ ነው
Apr 5, 2026 337
ጅግጅጋ፣መጋቢት 27/2018(ኢዜአ)፦የመጋቢት 24ቱ ለውጥ ሀገሪቷን ተደቅነውባት ከነበረ ውስጣዊና ውጫዊ ስጋቶች ያተረፈ ነው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር መሀመድ ሻሌ ገለጹ። የመጋቢት 24ቱ ሀገራዊ ለውጥ 8ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር መሀመድ ሻሌ በህዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ ላይ እንደገለጹት፣ የመጋቢት 24ቱ ለውጥ የክልሉ ሠላምና ልማት የተጠናከረበት እና ህብረ ብሔራዊ አንድነት የጎለበተበት ነው። በተለይም የሶማሌ ክልል ቀደም ሲል ከነበረበት የሠላምና ልማት ችግር ወጥቶ በሀገሪቱ ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎን ያረጋገጠበት ነው ብለዋል። እለቱ ኢትዮጵያን ተደቅነውባት ከነበረው ውጫዊና ውስጣዊ ስጋቶች ያተረፈ መሆኑን ገልጸው፤ መጋቢት 24 ክልሉም በሀገሪቷ ፖለቲካዊ እኩል ተሳትፎ ያሳደገበት መሆኑን ነው ያነሱት። በለውጡ አመታት በሀገሪቷ ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች የተጀመረበት እና የተጠናቀቀበት መሆኑንም ገልጸዋል። የጅግጅጋ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ሻፊ አህመድ በበኩላቸው፥ የመጋቢት 24 ለውጥ የዜጎች የሠላም፣የልማትና የመልካም አስተዳደር ተሳትፎ የተቀየረበትና የህዝቡን ችግሮች የፈቱ የልማት ሥራዎች የተከናወኑበት ነው ብለዋል። ከለውጡ በፊት ክልሉ የሠላም ፤ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ችግሮች የነበረበት እንደነበረ አንስተው፤ከለውጡ በኋላ ወደ ልማት በመግባት የብልጽግና ተምሳሌት ሆኗል ብለዋል። የክልሉ ህዝብ ከስጋትና ፍርሃት የወጣበትና የሀገሪቷ የፖለቲካ ተሳትፎ የጨመረበት መሆኑንም አክለዋል። ጅግጅጋ ከተማ የከተሞች ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷን በመጥቀስ በሀገራዊ ለወጡ የተገኘው ሠላም እና ልማትን ለማስቀጠል ህዝቡ ተሳትፎውን እንዲያስቀጥልም አሳስበዋል። በድጋፍ ሰልፉ ላይ መጋቢት 24 ታሪካዊ ቀን የሚታወስበት ነው፤ የድልም ትሩፋት የተገኘበትና ሠላማችን የተረጋገጠበት ቀን ነው የሚሉና ሌሎች መልዕክቶች ተላልፈዋል።
ይበጀናል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል - መራጮች
Apr 5, 2026 312
ጎንደር ፤ መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገር ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን አስተያየታቸውን የሰጡ የጎንደር ከተማ መራጮች ተናገሩ፡፡ የዲላ ከተማ ነዋሪዎች በጠቅላላ ምርጫው ድምፅ ለመስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ነው የጎንደር ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ገበያው ተረፈ ለኢዜአ እንደገለጹት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በምርጫ ተወዳድሮ የተመረጠ መንግስት ለሀገር እድገትና ብልጽግና መሰረት ነው። ይህን በመገንዘባቸውም ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ቀድመው በማውጣት የምርጫውን እለት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አስረድተዋል። የከተማዋ ነዋሪ ወጣት ፋሲል ጀመረ በበኩሉ ምርጫ የሀገራችንን የወደፊት እጣ ፈንታ የምንወስንበት መሆኑን ሁሉም ሰው ሊገነዘብ ይገባል ሲል ገልጿል። በዚህም ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው መምረጥ እንዲችሉ የምርጫ ካርድ ጊዜው ከማብቃቱ በፊት ማውጣት አለባቸው ብሏል። ምርጫ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ መሪውን ለስልጣን የሚያበቃበት በመሆኑ እኔም ባወጣሁት ካርድ የምፈልገውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ሲል ተናግሯል፡፡ ወይዘሮ ወርቄ ታደሰም ለሴቶች እኩልነት፣ መብትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የቆመ ፓርቲን ለመምረጥ የሚያስችለኝን የምርጫ ካርድ አውጥቻለሁ ብለዋል። ካርዴንም ለህዝቡ ኑሮ መለወጥ እንዲሁም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጥ እጠቀምበታለሁ ሲሉ ገልጸዋል። በሚዲያ እየተካሄደ ያለው ክርክር ፓርቲዎች ያላቸውን ፖሊሲና ፕሮግራም ለመገንዘብ እያስቻላቸው በመሆኑ በምርጫው እለት ድምጽ ለመስጠት እንደማይቸገሩ አስተያየት ሰጪዎች አረጋግጠዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገው የጊዜ ሰሌዳ ያመለክታል፡፡
የዲላ ከተማ ነዋሪዎች በጠቅላላ ምርጫው ድምፅ ለመስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ነው
Apr 5, 2026 251
ዲላ ፤ መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ መሆኑን የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ለዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን እያስተዋወቁ ሲሆን መራጮችም የምርጫ ካርዳቸውን በመውሰድ ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ የበኩላቸውን ለማበርከትና ዜግነት ሀላፊነታቸውን ለመወጣት እየሰሩ ናቸው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዲላ ከተማ ነዋሪዎች፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ በመስጠት ህገ-መንግሥታዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ እሸቱ ፀጋዬ በምርጫው በንቃት መሳተፍ የዜግነት ግዴታቸው መሆኑን አንስተዋል። የምርጫ ዴሞክራሲያዊነት የሚወሰነው በዜጎች ተሳትፎ ልክ በመሆኑ ለዚህም የምርጫ ካርድ በመውሰድ የድርሻቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። ይህም በቀጣይ አምስት ዓመታት በአግባቡ ይመረኛል፣ ይጠቅመኛል ብለው ያመኑበትን ፓርቲ ለመምረጥ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል። በምርጫው ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም ካርድ መውሰዳቸውን ያነሱት ደግሞ ወይዘሮ እመቤት ደበሌ ናቸው። ምርጫ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መንግስት የሚሰየምበት መሆኑን አንስተው ለዚህም የመራጭነት ካርድ በመውሰድ መምረጥ እንደሚገባም አንስተዋል። ሌላኛው የከተማው ነዋሪ ያውቃል ሞላ በበኩላቸው፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ይህም የፈለገውን እና ያመነበትን ፓርቲ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም እንደሚያስችላቸው ነው የጠቀሱት። ምርጫው ሠላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ድምፅ በመስጠት ህገ-መንግሥታዊ መብቱን ለመጠቀም መዘጋጀቱን ያነሳው ደግሞ ወጣት ልኡል በቀለ ነው። በምርጫው የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ የምርጫ ካርድ መያዝ ወሳኝ በመሆኑ የመራጭነት ካርድ መውሰዱን ተናግሮ ሌሎችም በቀሩት ቀናት ካርድ እንዲወስዱ ጠቁሟል።
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 14 ተራዘመ
Apr 4, 2026 1296
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሲያከናውን የቆየውን የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን አስታወቀ። ቦርዱ ቀደም ሲል ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲከናወን መታቀዱን አስታውሷል። የምዝገባ ሂደቱን በቴክኖሎጂ ለማገዝ በወጣው ዕቅድ መሠረትም የዕጩዎች ምዝገባ በአሁኑ ወቅት መጠናቀቁንና የመራጮች ምዝገባ ደግሞ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ሲከናወን መቆየቱን ገልጿል። ሆኖም በምዝገባ ሂደቱ ወቅት በተወሰኑ አካባቢዎች በቴክኖሎጂ የታገዘውን አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ የኔትወርክ አቅርቦት ችግር ማጋጠሙን ቦርዱ ገልጿል። ይህንን ተግዳሮት በመቅረፍ ሂደቱን አስተማማኝና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጠቀመውን ተጨማሪ ጊዜ ለማካካስ የምዝገባውን ጊዜ ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብሏል። በተጨማሪም አስተማማኝ የኔትወርክ አቅርቦት ይኖራቸዋል ተብለው በታሰቡ አንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የኔትወርክ መቋረጥ በማጋጠሙ፣ ሂደቱን ወደ ማኑዋል (በእጅ) አሠራር በመቀየር ረገድ የባከነውን ጊዜ ለመተካት መወሰኑን በመግለጫው አመልክቷል። በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች በነበረ የትራንስፖርት ችግር ምክንያት የምዝገባ ቁሳቁሶች በወቅቱ ባለመድረሳቸው ለተፈጠረው መዘግየት ምላሽ ለመስጠት፣ ቦርዱ የመራጮች ምዝገባው ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም ማድረጉን አስታውቋል።
መጋቢት 24 የሶማሌ ክልል ህዝብ ትክክለኛ ውክልና ያገኘበትና አዲስ የፖለቲካ ባህል የታየበት ዕለት ነው
Apr 4, 2026 721
ጅግጅጋ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ መጋቢት 24 የሶማሌ ክልል ህዝብ ትክክለኛ ውክልና ያገኘበትና አዲስ የፖለቲካ ባህል የታየበት ዕለት ነው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ገለጸ። የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ኢንጂነር መሀመድ ሻሌ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ መጋቢት 24 የሶማሌ ክልል ህዝብ ትክክለኛ ውክልና ያገኘበትና አዲስ የፖለቲካ ልምምድ የጀመረበት ዕለት ነው ብለዋል። ከለውጡ የሶማሌ ክልል የሠላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ችግሮች የነበሩበት መሆኑን አስታውሰው ከለውጡ ወዲህ ለችግሮቹ መፍትሄ በመገኘቱ በክልሉ አሁን ላይ ውጤታማ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። በለውጡ ዓመታት በተከናወኑ ሪፎርሞች በክልሉ ሁለንተናዊ ልማት እየተረጋገጠ መሆኑን ገልፀው ከአግላይና ከፋፋይ የፖለቲካ ሥርዓት በመውጣት አዲስ የፖለቲካ ባህል መታየቱንም አክለዋል። በአሁኑ ወቅት መንግስትና ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር በመስራት ላይ እንደሚገኙ አንስተው በክልሉ በተፈጠረው ምቹ የፖለቲካ ምህዳር በጠቅላላ ምርጫው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚወዳደሩም ገልጸዋል። በጸጥታና በፍትህ ተቋማት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውንና የማጠናከር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በክልሉ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸውን በመጥቀስ በቀጣይም በክልሉ የሚገኙ ፀጋዎችን በተገቢው መንገድ መጠቀም የሚያስችሉ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። በክልሉ ተግባራዊ የተደረጉ አዳዲስ ኢኒሼቲቮች ዘርፈ ብዙ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸው ህብረተሰቡን በሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራት ይጠናከራሉ ብለዋል። ክልሉን የቱሪዝም የስበት ማዕከል ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች በውጤታማነት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ማህበረሰቡን ከተረጂነት ለማውጣት የተጀመሩ የግብርና ልማት ሥራዎች የበለጠ እንደሚጠናከሩም አረጋግጠዋል።
ማህበራዊ
አዲስ ስፖርት ፓርክ ለአትሌቶች የሚገባው ክብር የተሰጠበት ታሪካዊ ስራ ነው
Apr 5, 2026 108
አዲስ አበባ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ ስፖርት ፓርክ፣ ለሀገር ክብር የደከሙ ጀግኖች አትሌቶችን የሚዘክርና ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ ተነሳሽነት የሚፈጥር መሆኑን አትሌቶች ገለጹ። አዲስ ስፖርት ፓርክ ጀግኖችን ያከበረ ማዕከል ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአዲስ ስፖርት ፓርክን ትናንት መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መርቀው ለህዝብ ክፍት አደርገዋል። በዚሁ ወቅትም የአዲስ ስፖርት ፓርክ የመዲናዋን ዕድሳት በማፋጠን የዜጎችን ክብር ለመመለስ የተገባው ቃል መተግበሩን አንዱ ማረጋገጫ እንደሆነ ገልጸዋል። በአምስት ነጥብ ሰባት ሄክታር መሬት ላይ ባረፈው ፓርክም በዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ መድረክ ኢትዮጵያን ክብር ያጎናጸፉ 15 ጀግና አትሌቶች ሐውልት ቆሞላቸዋል። ለተተኪ ትወልድ በትዕምርትነት የሚያገለግለው ፓርክ ዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ ደረጃን ያሟሉ ዘመናዊ የመዋኛ ገንዳ፣ የእግርና የቅርጫት ኳስ፣ የቴኒስና የሩጫ ትራክና ሜዳዎችን የያዘ ማዕከል ነው። በአዲስ ስፖርት ፓርክ ሐውልት የቆመላቸውና በምርቃቱ ላይ የታደሙ አንጋፋና ወጣት አትሌቶች ፓርኩ መገንባቱ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረላቸው ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል። አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በሰጠው አስተያየት፤ ቀደም ሲል በውጭ ሀገራት የሚያዩዋቸውን መሰል ዘመናዊ ስፍራዎች ሀገር ውስጥ ተገንብቶ በማየቱ ታላቅ ደስታ ተሰምቶኛል ብሏል። አዲስ አበባን ሳቢ በማድረግ በምሽት ጭምር አገልግሎት የሚሰጡ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጿል። በዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ መድረክ የሀገራቸውን ክብር ከፍ ላደረጉ ጀግና አትሌቶች የመታሰቢያ ሐውልት መቆሙም ከፍተኛ ኩራት እንደተሰማው በመግለፅ፤ ለዚህም ምስጋና አቅርቧል። አትሌት ገዛኸኝ አበራ እንደገለጸው፤ በእነርሱ ዘመን ያልነበሩ ዘመናዊ የሩጫ ትራኮች አሁን ላይ በስፋት መገንባታቸው የተተኪ ስፖርተኞችን ችግር ያቃልላል። መንግሥት ለአትሌቶች በሰጠው ክብር አመስግኖ፣ ኢትዮጵያ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ የሚያስችሏት የመሠረተ ልማት ሥራዎች መከናወናቸው የሚደነቅ መሆኑን ተናግሯል። ኢትዮጵያ በሰራቻቸው የስፖርት ፓርክና የኮሪደር ልማት በሌሎች አገራት አድናቆት እያገኘች መምጣቷንም ገልጿል። "በህይወት እያለሁ ታሪኬን የሚዘክር ሐውልት በመቆሙ ዳግም እንደተወለድኩ ሆኖ ተሰምቶኛል" ያለው ኮማንደር አትሌት ታምራት ቶላ፤ ለመንግስት ምስጋናውን አቅርቧል። አሁን ላይ በስፋት የተገነቡ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የመሮጫ ትራኮችን ወጣቱ በአግባቡ በመጠቀም የሀገሩን ስም እንዲያስጠራ አትሌቱ ጥሪ አቅርቧል። ኮማንደር አትሌት ሰለሞን ባረጋም በኦሎምፒክ መድረኮች ብቻ የሚታዩ ጥራት ያላቸው ስራዎች በሀገሩ በመገንባታቸው የተሰማውን ኩራት ገልጿል። ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ያላትን ፀጋ አልምቶ ለመጠቀም መንግስት የጀመረው ስራ ታላቅ ተምሳሌት መሆኑን አትሌቶቹ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን በበኩሉ፤ መንግስት ለስፖርት ማዘውተሪያዎች የሰጠው ትኩረት ለዘርፉ ዕድገት አዲስ ዕድል መፍጠሩን ገልጿል። እንደ አደይ አበባ ስታዲየም እና አዲስ ስፖርት ፓርክ ያሉ ግዙፍ ግንባታዎች ኢትዮጵያ የዓለም ሻምፒዮናዎችን በልበ ሙሉነት እንድታስተናግድ የሚያስችሏት መሆኑንም ጠቁሟል። ይህ በምሽትም ጭምር የሚያገለግለው ዘመናዊ መሰረተ ልማት አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ይበልጥ ተስማሚና ሳቢ ከማድረጉም በላይ ለስፖርቱ እድገት አዲስ ተስፋ የፈነጠቀ መሆኑንም ተናግሯል።
አዲስ ስፖርት ፓርክ ጀግኖችን ያከበረ ማዕከል ነው
Apr 5, 2026 164
አዲስ አበባ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በአዲስ አበባ ዑራኤል አካባቢ የተገነባው የአዲስ ስፖርት ፓርክ የስፖርቱን ዘርፍ የዘመናት መሻት እውን ያደረገ ድንቅ የሥራ ውጤት ሆኗል። አዲስ ስፖርት ፓርክ ለአትሌቶች የሚገባው ክብር የተሰጠበት ታሪካዊ ስራ ነው የአዲስ ስፖርት ፓርክም ስሙ ብቻ ሳይሆን ይዘቱም አዲስ ነው። ኢትዮጵያ ለጀግኖቿ ያላትን ክብር የገለጸችበት፣ለተተኪዎቿም የተስፋ ብርሃን የለኮሰችበት የስፖርት አውድ ለመሆን በቅቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትናንት መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መርቀው የከፈቱት ይህ ፓርክ፣ የመወዳደሪያ ስፍራ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ሁሉን አቀፍ ልማት ጉዞ እንደሚያሳይ ተገልጿል። በፓርኩም የስፖርት መሠረተ ልማት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አደባባይ በአንጸባራቂ ድሎቻቸው ያውለበለቡ ድንቅ የአትሌቲክስ ፈርጦች ሐውልት ቆሟል። በዚህ ታሪካዊ ስፍራ ሐውልት ከቆመላቸው 15 የኢትዮጵያ እንቁ አትሌቶች መካከል ስድስቱ እንስት ጀግና አትሌቶች ሃሳባቸውን አጋርተውናል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፈር ቀዳጇ አትሌት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፤ ፓርኩን ስትመለከት የታያት የሀገር ከፍታ ነው። "እንዲህ ዓይነት ፓርክ በውጭ ሀገር ስንመለከት እንመኘው ነበር፤ ዛሬ በሀገራችን ተሰርቶ ማየቴ ታላቅ ደስታ ነው" ትላለች። አትሌት ደራርቱ አክላም፣ ፓርኩ የኢትዮጵያን የኦሎምፒክ ተሳትፎ እንደሚለውጥ ገልጻ፤ "እኛ በባዶ እግር ነው የጀመርነው፤ አሁን ግን መሰረተ ልማት ተሟልቶ በፕሮፌሽናል ደረጃ መሰልጠን ተችሏል።እንዲህ ያሉ ስራዎች ከተጠናከሩ 15 ሳይሆን 15 ሺህ ወርቅ እናመጣለን" ስትል ለወደፊቱ ትውልድ ያላትን ትልቅ ተስፋ አጋርታለች። የማራቶን ድል አድራጊዋ አትሌት ኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ በፓርኩ ውስጥ የቆመው ሐውልት ትርጉም በቃላት የማይገለጽ መሆኑን ትናገራለች። "ሐውልታችን መቆሙ ለእኛም ሞራል ለሚቀጥለው ትውልድም ትምህርት ነው" የምትለው ፋጡማ፣ይህ ስፍራ ለልጅ ልጅ የሚተርፍ የስኬት ማስታወሻ መሆኑን ገልጻለች። በውጭ ሀገራት የምናያቸው ጥራት ያላቸው የስፖርት ፓርኮች ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር ላይ መገንባታቸው ለስፖርቱ እድገት አቅም እንደሚሆንም አብራርታለች። የረጅም ርቀት ንግሥቷ ኮማንደር ጥሩነሽ ዲባባ፣የሐውልቱን መቆም ከሀገር ክብርና ከትውልድ ቅብብሎሽ ጋር አስተሳስራዋለች። ድሮ እኛ በነባር አትሌቶች ተነሳስተን ነው እዚህ የደረስነው የምትለው ደማቋ አትሌት፥ ዛሬ ደግሞ ተተኪዎች የእኛን ሐውልት ሲያዩ ለታላቅነት መነሳሳት ይፈጥርላቸዋል ትላለች። ጀግኖችን በሕይወት እያሉ ማክበር ለሚመጣው ትውልድ ለሀገሩ ትልቅ ሥራ እንዲሠራ መነሳሳት የሚፈጥርና ምሳሌ እንደሚሆንም በኩራት ገልጻለች። ለአትሌት መሰረት ደፋር አዲስ ስፖርት ፓርክ ማመን እስኪያቅታት ነው የሆነባት። "ቃላት ያጥረኛል" የምትለው አትሌቷ፤ ኡራኤል አካባቢን በዚህ ገጽታ አየዋለሁ ብዬ አላመንኩም በማለት ነበር ስሜቷን የገለጸችው። አትሌት መሰረት ቀደም ሲል በአዲስ አበባ መሮጫ ስፍራ እንኳን እንዳልነበረ አስታውሳ፤ አሁን ግን ህዝቡ ጤናውን የሚጠብቅበት ውብ ቦታ መዘጋጀቱን ታደንቃለች። አልባሌ ቦታ ከመዋል እዚህ መጥቶ ሀገርን ለማስጠራት መስራት ይገባል በማለትም ለወጣቶች ጥሪዋን አስተላልፋለች። አትሌት ሃምሳ አለቃ አልማዝ አያና በበኩሏ የፓርኩን ጥራትና ምሉዕነት አድንቃለች። "ምንም እንከን የሚወጣለት ነገር የለም፤ ይህ ልዩ ነው" የምትለው አትሌት አልማዝ፣ፓርኩ ስፖርት አቁመው የነበሩትን እንኳን ዳግም ወደ ሜዳ እንዲመለሱ የሚያደርግ እንደሆነ ትገልጻለች። በመንግሥት ለስፖርት ዘርፉ የተሰጠ ትልቅ ሥፍራ መሆኑንም ትመሰክራለች። አትሌት መቶ አለቃ ቲኪ ገላና ፓርኩ ሁሉንም ስፖርት በአንድ ማዕከል መያዙ ልዩ ያደርገዋል ብላለች። ለሀገር አቋራጭ መሮጫ የሚሆን ስፍራ፣ የዋና፣ የእግር ኳስና ሌሎች ስፖርቶችን መሠረተ ልማት ማካተቱ ለኢትዮጵያ ስፖርት ከፍታ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ጠቁማለች። አትሌቶቹ አዲስ ስፖርት ፓርክ የኢትዮጵያን የነገ ተስፋ በፅኑ መሰረት ላይ የጣለ ታላቅ ስራ መሆኑን ገልጸዋል።
በሐረሪ ክልል በለውጡ ዓመታት ሁሉንም ዜጎች ተጠቃሚ ያደረጉ ስራዎች ተከናውነዋል
Apr 5, 2026 73
ሐረር ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል በለውጡ ዓመታት ሁሉንም ዜጎች ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ። በሐረሪ ክልል ሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ ማደራጃ ማዕከል በሙሉ አቅሙ ተደራጅቶ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። በከተማው በሚገኘው አብርሃ ባህታ የተሃድሶ ህክምና ማዕከል የሚገኘው ሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ ማደራጃ ማዕከል ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት አቋርጦ የነበረ ሲሆን የክልሉ ጤና ቢሮ በሰው ሃይልና ቁሳቁስ ዳግም በማደራጀት በአዲስ መልክና በሙሉ አቅም ለአገልግሎት አብቅቷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማና በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማህበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሁርያ አሊ ማዕከሉን መርቀው ስራ አስጀምረዋል። ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በወቅቱ እንደገለፁት፤ በክልሉ ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ የልማት ተግባራት ተከናውነዋል። በክልሉ የተከናወኑ ስራዎችም ክልሉን ወደ ተሻለ የእድገት ደረጃ ያሻገሩና የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆኑን አመልክተዋል። አክለውም የአካል ጉዳት ተጎጂ የሆኑ ዜጎችን የመደገፍ፣ የመንከባከብና በልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራም ተከናውኗል ብለዋል። በክልሉ የነበረው የሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ ማደራጃ ማዕከል ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት ሳይሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው በአሁኑ ወቅት ማዕከሉ እንደገና አገልግሎት መጀመሩ የአካል ድጋፍ ህክምና የሚፈልጉ ተገልጋዮችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ማዕከሉ በዘላቂነትና ቀጣይነት ባለው መልኩ አገልግሎት እንዲሰጥ መንግስት ከሚያከናውነው ስራ ጎን ለጎን ባለድርሻ አካላትም አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ ይገባል ብለዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ እንደገና አገልግሎት መስጠት መጀመሩ አበረታች መሆኑን ጠቅሰዋል። ከዚህ ጎን ለጎን ማዕከሉ የተሟላና ሁሉንም ዓይነት የጤና አገልግሎቶች እንዲሰጥ የማስቻል ስራ በቀጣይ ይከናወናል ብለዋል። በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማህበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሁርያ አሊ፤ ማዕከሉ በአዲስ መልክ ታድሶና ተገቢው ግብዓት ተሟልቶለት ወደ ስራ እንዲገባ መደረጉ የሚያስደስት ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። ማዕከሉ አካል ጉዳተኞች የሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ በማደራጀት በልማቱ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል። በቀጣይም በክልሉ ኤረር ወረዳ ኡላን ኡላ ቀበሌ የተገነባውን 2ኛ ደረጃ ጤና ኬላን መርቆ አገልግሎት የማስጀመርና በድሬ ጠያራ ወረዳ አዲስ ለሚሰራው የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነ ስርዓት ይካሄዳል።
የታዳሽ ሃይልን በመጠቀም ለገጠሩ ህብረተሰብ የሃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቷል
Apr 5, 2026 127
ባህርዳር ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦ የታዳሽ ሃይልን በመጠቀም የገጠሩን ህብረተሰብ የሃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት መስጠቱን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ "በብሄራዊ የኤሌክትሪፍኬሽን ፕሮግራም" አተገባበር ላይ ያተኮረ የሁለት ቀናት ስልጠና በባህርዳር ከተማ አስጀምሯል። በሚኒሰቴሩ የኢነርጂ ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ኢንጅነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለፁት ኢትዮጵያ በሃይድሮ፣ በፀሃይ፣ በነፋስና በጂኦተርማል ሃይል ማመንጨት የሚያስችል ከፍተኛ አቅም አላት። ከነዚህ ዘርፎች ብቻ 150 ጊጋ ባይት ሃይል የማምረት አቅም ያላት ቢሆንም እስካሁን ወደ ልማት የገባው ግን ስድስት በመቶው ብቻ መሆኑን ገልፀዋል። ይህን የመልማት አቅም ወደ ውጤት ለመቀየር ከተደረጉ ጥረቶች መካከል ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና ሌሎች ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተዋል። የታዳሽ ሃይልን በመጠቀም የገጠሩን ህብረተሰብ የሃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን አስታውቀዋል። ሀገሪቱ ለጀመረችው ፈጠን እድገት የሚያስፈልግን የሃይል አቅርቦት ለማሳካትና ብሄራዊ "የኤሌክትርፍኬሽን ፕሮግራም" ትግበራን በሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ ለታዳሽ ሃይል ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል። በተለይም በፀሃይ ሃይል የሚሰሩ የሃይል አማራጮችን በስፋት በገጠሩ ለሚኖረው ህብረተሰብ ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ሂደት የዛሬው ስልጠና አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል። የአማራ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ሃላፊ ኢንጅነር ዳኝነት ፈንታ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የሃይል አቅርቦትን ተደራሽነትን በማሳካት የክልሉን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ለማፋጠን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። ይህም ከተሞችን ለማዘመን፣ ኢንዱስትሪዎችና ሌሎች ኢንቨስትመንቶችን ለማስፋፋት መሰረት በመሆን የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተጨማሪ አቅም ይሆናል ብለዋል። በክልሉ በተራራቀ አሰፋፈር የሚኖረውን የገጠሩን ማህበረሰብ የሃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ በፀሃይ ሃይል ለሚሰሩ የኤሌክትሪክ መሰረት ልማት ዝርጋታ ላይ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚሁ ስልጠና የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የሶላር ፓኔል አቅራቢዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ኢኮኖሚ
የግብርናው ዘርፍ እመርታ በቤተሰብ ደረጃ የአርሶና አርብቶ አደሩን ብልፅግና እያረጋገጠ ነው
Apr 5, 2026 98
አዲስ አበባ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦የግብርናው ዘርፍ እመርታ በቤተሰብ ደረጃ የአርሶና አርብቶ አደሩን ብልፅግና እያረጋገጠ እንደሚገኝ የክልል የግብርና ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ የልማት አቅጣጫ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችል ታሪካዊ ስኬት እያስመዘገበ ይገኛል። ለአብነትም በበጋ መስኖ ስንዴ፣ በሌማት ትሩፋት፣ በመኸርና በበልግ የሰብል ምርታማነት ወቅቶች የአርሶና አርብቶ አደሩን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ከፍተኛ ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የኢትዮጵያን የተመፅዋችነት የታሪክ ስብራት በማረም ከራስ አልፎ ስንዴን ለውጭ ገበያ ማቅረብ ያስቻለ አቅም ፈጥሯል። የክልል ግብርና ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ለኢዜአ እንዳሉትም፤ በከተማና ገጠር በግብርና ዘርፍ የተፈጠረው የምርታማነት አቅም የአርሶና አርብቶ አደሩን የኑሮ ደረጃ እያሻሻለ ነው። በሀገራዊ ለውጡ ማግስት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተተገበሩ የግብርና ምርታማነት ተነሳሽነቶችም የምግብ ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ መሰረት መጣላቸውን ገልጸዋል። የአርሶና አርብቶ አደሩ ዘመናዊ የምርታማነት ሥርዓትም የግብርና ሽግግርን በማፋጠን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አሕመድ ሃቢብ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ለውጡ የግብርና ዘርፉን በማዘመን የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ጉዞ እያፋጠነ ነው። የብዝኅ ዘርፍ የኢኮኖሚ ልማት አቅጣጫዎችም የግብርና ሽግግርን በማሳለጥ በቤተሰብ ደረጃ የተሟላ ብልፅግናን እያረጋገጡ መሆኑን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ተግባራዊ የተደረጉ የአርሶና አርብቶ አደሩን ግብርና የማዘመን የልማት መርሃ ግብሮችም እመርታዊ ስኬት ማስገኘታቸውን አስረድተዋል። በቀጣይም በሌማት ትሩፋትና በሰብል ምርታማነት የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠል የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ሥራ ለማፋጠን በትኩረት እንደሚሰራ አንስተዋል። በአፋር ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አሕመድ አሚን በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ለውጡ የኢትዮጵያን ግብርና ከዝናብ ጥገኝነት ማላቀቅ ያስቻለ ስኬት አስገኝቷል ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋትና የስንዴ ልማት መርሃ ግብሮች የክልሉን ከፊል አርሶና አርብቶ አደር ማህበረሰብ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ምርታማነትን እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። የኩታ ገጠም ሜካናይዜሽን የእርሻ ልማት መርሃ ግብርም የግብርና ግብዓት አቅርቦት ሰንሰለትን በማሳለጥ ወሳኝ የምርታማነት አቅም እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ምርት በዓለም አቀፍ ገበያ ከፍተኛ ዕድገት እያስመዘገበ ነው
Apr 5, 2026 231
አዲስ አበባ፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ የአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዘርፉን ዓለም አቀፍ የገበያ ተወዳዳሪነት ማሳደጉን አምራችና ላኪዎች ገለጹ። የሆርቲካልቸር ዘርፍ የዓለም አቀፍ ገበያ የተወዳዳሪነት አቅም ከቡና ቀጥሎ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ገቢ በማስገኘት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የድርሻውን እያበረከተ ይገኛል። የአበባ፣የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ የተሰማሩ አምራቾች ለኢዜአ እንዳሉት፤በሀገራዊ ለውጡ ማግስት የዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነትን እያሳደገ ነው። የኢቲ ሃይላንድ ፍሎራ አበባ አምራችና ላኪ ሥራ አስኪያጅ እመቤት ተስፋዬ፤ ለሆርቲካልቸር የተሰጠው ትኩረት የአበባ ምርታቸውን በአውሮፓና አሜሪካ ገበያ የሚያቀርቡበት ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። የኢትዮጵያ የአበባ ምርት የዓለም አቀፍ የገበያ ተፈላጊነት እያደገ መምጣቱም ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ከቲንግ ሲንጀንታ ፍላወር ሳይት ማናጀር መስፍን ግርማ በበኩላቸው፥የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በተለያዩ ክፍለ አህጉራት ያለው ከፍተኛ ተፈላጊነት የገበያ መዳረሻ ዕድልን አስፍቷል ብለዋል። በመንግስት በኩል በመሬት አቅርቦትና ተያያዥ መሠረተ ልማት ግንባታ የተሰጠው ትኩረት ምርታማነትን በማሳደግ የገቢ አቅም እያጎለበተ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም የአበባ ምርታማነት አቅምን በማስቀጠል በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካኝነት ምርትን በጥራትና በፍጥነት ለዓለም ገበያ ለማቅረብ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የሬድ ፎክስ ኢትዮጵያ ዱመኖሬንጅ አበባ ላኪ ማናጀር ራሄል ክፍሌ በበኩላቸው፤አውሮፓ፣ አሜሪካና የእስያ ገበያ የኢትዮጵያ የአበባ ምርት ወሳኝ የገበያ መዳረሻዎች ናቸው ብለዋል። ይህም የውጭ ምንዛሬ ገቢን በማሳደግ የአበባና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ እንዲጎለብት እያስቻለ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወንዳለ ሃብታሙ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የኢትዮጵያን የሆርቲካልቸር ዘርፍ ኢንቨስትመንትና ምርታማነት የሚያጎለብት ምቹ ምኅዳር ተፈጥሯል ብለዋል። በዚህም የኢትዮጵያ ሆርቲካልቸር በዓለም ገበያ ያለው ተፈላጊነት የውጭ ምንዛሬ ገቢን በማሳደግ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ የላቀ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በአበባ፣አትክልትና ፍራፍሬ ወጪ ንግድ የምታስገኘው ስኬት የሥራ ዕድል ፈጠራና መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግርን እያፋጠነ መሆኑን አንሰዋል።
የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች
Apr 5, 2026 2375
በዮሐንስ ደርበው ✍️ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ‘በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ’ ከሚለው ብኂል የላቁና ቁጭት የወለዳቸው ኢኒሼቲቮች - የቱሪዝም ፀጋን ከመግለጥ ባለፈ የገቢ መጠንን እንዲሁም የሥራ ዕድልን እያሳደጉ ነው። ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ እንደመሆኗ ብዙ ናት። ይህን ሁሉም ሀገራት ስለማያገኙት ዕድለኛም ናት፤ የእኛም ስለሆነች መታደል ነው። የተለያየ የኑሮ ዘይቤ፣ ባህል እንዲሁም ሁሉንም የዐየር ፀባይ ዐቅፋለች። ደግሞም ልዩ ልዩ የተፈጥሮ አቀማመጥ በልዩነት የተቸራት። አሥረጂ ማቅረብ ቢያሻ በሀገሪቱ ከፍተኛ ከሆነው ስሜን ተራራዎች እስከ ዝቅተኛው ስፍራ ዳሎል ያለውን የተፈጥሮ ፀጋ መጥቀስ ሁነኛ ምሥክር ነው። ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ✍️ የተፈጥሮ ችሮታ ለኢትዮጵያ ከብዙ ሥጦታዎቿ መካከል ብሔራዊ ፓርኮችን ብቻ ብናነሳ… የኢትዮጵያ የዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን በጀት መድቦ በቀጥታ በሥሩ 11 ብሔራዊ ፓርኮችን እና ሁለት የዱር እንስሣት መጠለያዎች ያሥተዳድራል። እነሱም፡- 📌 ስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አብያታ ሻላ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ኦሞ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አልጣሽ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ገራይሌ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ሃላይደጌ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ቃፍታ ሽራሮ ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም 👉 ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ እና 👉 ሲንቂሌ የቆርኬዎች መጠለያዎች ናቸው። ብሔራዊ ፓርኮቹና የዱር እንስሣት መጠለያዎቹ የሀገሬው ሀብት ናቸውና፤ እየተንከባከቡ መጠቀም ይገባል። ✍️ መንግሥት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ከላይ የተገለጹትን ብሔራዊ ፓርኮችና ሌሎችንም፤ ከቤት እንስሣት ንክኪ ነጻ በማድረግ፣ ከልቅ ግጦሽ እንዲሁም ከሕገ-ወጥ ዐደን ለመጠበቅ መንግሥት ብዙ ገንዘብ ያወጣል። የሰው ኃይልና የቁሳቁስ ዐቅርቦትንም ያሟላል። ይህም ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ይመሠክራል። በሌላ በኩል የላሊበላ አብያተክርስቲያናት፣ ሶፍዑመር ዋሻን እና የፋሲል አብያተ መንግሥትን ጨምሮ በየክልሎች የሚገኙ ቅርሶችን በመጠገንም እንዲሁ እየተጋ ነው። ከአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎቹ አንዱ የቱሪዝም ዘርፍ ማድረጉም ትኩረቱን ያሳያል። በዚህ ሂደት በየአካባቢው ፀጋዎችን ዕየለየ በርካታ መዳረሻዎችንና የጎብኝ ማረፊዎችን አልምቷል፤ እያለማም ነው። እነዚህም በኢኮኖሚው ብሎም በሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍ ያለ ሚና እያበረከቱ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት፤ በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ የተሠሩ መዳረሻዎችን ለአብነት ብንጠቅስ፤ ‘በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ’ ከሚለው ብኂል የላቁና ቁጭት የወለዳቸው ኢኒሼቲቮች ናቸው። የቱሪዝም ፀጋን ከመግለጥ ባለፈ የገቢ መጠንን እንዲሁም የሥራ ዕድልን እያሳደጉ ነው። ኢትዮጵያ ዛሬ ነገንም እየሠራች ነውና፤ በቱሪዝሙ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት በተለያየ የኢትዮጵያ ክፍሎች መጭውን ትውልድ ባገናዘበ ሁኔታ እየተሳለጡ ነው። በአፍሪካ መዲና በአንድነት እና የወዳጅነት ፓርኮች ጅማሮውን ያደረገው የዘርፉ ልማት፤ ወደ ወንጪ ኢኮቱሪዝም፣ ጎርጎራ፣ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት፣ የሸበሌ ሪዞርት፣ ሶፍዑመር ዋሻ፣ ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፣ የዝሆኖች ዳና ሎጂ፣ የኒዒን ሌ ፓልም ሎጂ ድረስ ወዘተ… ዘልቋል። እንደቀጠለም ነው። እነዚህም ፀጋን ለይቶ ወደ ሃብት በመቀየር ሂደት በመንግሥት ብርታት የለሙ መዳረሻዎች ናቸው። መንግሥት ነባር መዳረሻዎችን በመጠገንና በማደሥ፤ አዳዲስ መዳረሻ በመገንባት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም አልሠሠተም፤ ብዙ እየሠጠ ነው። ✍️ ከቱሪዝም ዘርፍ አንጻር የሕብረተሰቡ ሚና ቱሪዝም በተፈጥሮው ከበርካታ ጉዳዮች ጋር ይተሣሠራል። በእጅጉ ሰላም ይሻል፤ የሰላም ባለቤት ደግሞ ሕዝቡ ነው። ዘርፉ የቅርሶችንና መዳረሻዎችን ልማትና እንክብካቤም ይሻል። ለዘርፉ የሚሰጥ ትኩረት ሀገርንም፤ ሕዝብንም ይጠቅማል፤ ጥቅሙ ከዕለት ጉርስ እስከ ጥሪት ይዘልቃል። በዚህ ሂደት ሕዝቡ በየአካባቢው ያሉ ብሔራዊ ፓርኮችን፣ ቅርሶችን እና የቱሪስት መዳረሻዎችን የኔ ብሎ መጠበቅ ይኖርበታል። ለምሳሌ፡- ብሔራዊ ፓርክ ወይም በመዳረሻ ላይ ጉዳት ቢደርስ በቀጥታ ተጎጂው የአካባቢው ነዋሪ ነው። ምክንያቱም ቱሪስት ካልሄደና ገቢ ካልተገኘ ገቢ ይደርቃልና።
የነዳጅ አቅርቦት ጫናን ለመቋቋም መንግስት ያሳለፈውን ውሳኔ መሰረት በማድረግ ምርትን በፍትሐዊነት እያከፋፈልን ነው
Apr 5, 2026 103
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ሁኔታን ተከትሎ የነዳጅ አቅርቦት ጫናን ለመቋቋም መንግስት ያሳለፈውን ውሳኔ መሰረት በማድረግ ምርትን በፍትሐዊነት እያከፋፈሉ እንደሚገኝ የነዳጅ ማደያዎች ገለጹ። በነዳጅ አቅርቦት ላይ የተፈጠረውን ችግር ለመቋቋም የተቀመጡ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በአግባቡ እንተገብራለን -አሽከርካሪዎች የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በአዲስ አበባ የተለያዩ የነዳጅ ማደያዎች ባደረገው ቅኝት፤ ማደያዎቹ የሚራገፈውን ነዳጅ በፍትሐዊነት ለተጠቃሚዎች እያከፋፈሉ እንደሚገኙ ተመልክቷል። የመካከለኛው ምስራቅ ግጭትን ተከትሎ በርካታ የዓለም ሀገራት በነዳጅ አቅርቦት ላይ የተፈጠረውን መስተጓጎል ለመቋቋም ጥብቅ የቁጠባ መመሪያዎችን በማውጣት ላይ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በወቅታዊ ሁኔታው ሳቢያ በነዳጅ አቅርቦት ሰንሰለት ላይ የተፈጠረውን ችግር ለመቋቋም ዜጎች ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀሙ ማሳሰባቸው ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የአቅርቦት ሰንሰለቱን በቁጠባና በጥብቅ ቁጥጥር መምራት የሚያስችል የተፅዕኖ መቋቋሚያ ውሳኔዎችን አስተላልፏል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፤ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ይፋ እንዳደረጉት፤ በነዳጅ አጠቃቀም ረገድ ለሚከተሉት ዘርፎች ቅድሚያ እንዲሰጥ መመሪያ ተላልፏል፦ በዚህም መሠረት፡-ነዳጅ የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች በማደያ የቅድሚያ ቅድሚያ እንዲሰጣቸው፤ ከፍተኛ አምራችና የኤክስፖርት ድርጅቶች በቀጥታ፣ ልዩ ትኩረት የሚሹ የመንግሥትና የግል ፕሮጀክቶች በቀጥታ፣ የገቢና ወጪ ንግድን ጨምሮ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች ግብርናን የሚያዘምኑ ትራክተሮች፣ የከተማና ሀገር አቀፍ የብዙሃን ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች እንዲሁም በናፍጣ የሚሰሩ ሌሎች ለህብረተሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች በቅድሚያ እንዲያገኙ የሚያደርግ የቅድሚያ የነዳጅ አጠቃቀም አሠራር የሚተገበር መሆኑን መግለፃቸው ይታወቃል። የገርጂ ኖክ ነዳጅ ማደያ ሥራ አስኪያጅ መልካሙ ሲያልፍ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ማደያው በመንግሥት የወረዱ መመሪያዎችን በአግባቡ በመተግበር ላይ ይገኛል። በተለይም ቅድሚያ እንዲሰጣቸው ለተወሰነላቸው ድርጅቶች ሕጋዊነታቸውን በማረጋገጥ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። በካዛንቺስ የኦላ ነዳጅ ማደያ ሠራተኛ መሰረት ወንድም በበኩላቸው፤ ለኅብረተሰቡና ለሀገር ልማት ወሳኝ ለሆኑ አካላት በወጣው አሠራር መሠረት ምርቱን እያቀረቡ መሆኑን አብራርተዋል። የሰባራ ባቡር ቶታል ነዳጅ ማደያ ሱፐርቫይዘር ባዬ መኮንን፤ ነዳጅን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በፍትሐዊነት እያከፋፈሉ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ሚኒስቴሩ ኅብረተሰቡ ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀም፣ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን እንዲከተልና የእግር ጉዞ ባህልን እንዲያጎለብት ጥሪ አቅርቧል። በተጨማሪም የሕዝብ ትራንስፖርትን በመጠቀምና በነዳጅ ግብይት ላይ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ ተግባራትን በማጋለጥ ረገድ ዜጎች ከመንግሥት ጋር ተባብረው እንዲሠሩ ማሳሰቡ ይታወሳል። የማደያዎቹ የሥራ ኃላፊዎችም በመካከለኛው ምስራቅ የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ በሀገር ላይ የሚኖረውን አሉታዊ ጫና ለመቀነስ ሁሉም ሰው በኃላፊነት ስሜትና በትዕግሥት ሊንቀሳቀስ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ዩኒቨርሲቲው የአፈር ለምነትን መጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቷል
Apr 4, 2026 225
ወላይታ ሶዶ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአፈር ለምነትን መጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። በዩኒቨርሲቲው "የአፈር ለምነትንና ጤናማነትን ማስጠበቅ ለግብርና ሽግግር" በሚል መሪ ሃሳብ 14ኛው ዙር ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ተካሂዷል። በወቅቱ በዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት አክበር ጩፎ(ዶ/ር) እንደገለፁት፤ ዩኒቨርሲቲው የአፈር ለምነትን መጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛል። የአፈር ለምነትና ጤናማነትን መጠበቅ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድግ በመሆኑ ለግብርና ዘርፍ ምርምሮች ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። በመሆኑም ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን በዘርፉ የተሰማሩ ተመራማሪዎችን በመደገፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በበጀት ዓመቱ ከ79 ሚሊየን ብር በላይ በጀት በመመደብ ከ50 በላይ የምርምር፣ 54 የማህበረሰብ ተኮር እንዲሁም ከ14 በላይ የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን እየሰራ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ(ዶ/ር) ናቸው። በዩኒቨርሲቲው ያለውን ዕውቀት ከሀብት ጋር ለማቀናጀት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ስለመሆኑም ገልጸዋል። በዚህም የዘንድሮው 14ኛው ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንስ የአፈር ጤንነትና ምርታማነት ላይ አተኩሮ መዘጋጀቱን ጠቁመው በዘርፉ የተሰማሩ ምሁራንና ባለሙያዎች ቅንጅታቸውን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል አበክረው መስራት እንዳለባቸውም አመልክተዋል። በዩኒቨርሲቲው የአፈር ሳይንስ ጥናት ፕሮፌሰር ፋኑኤል ላዕከማርያም ፅሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት በአፈር ዙሪያ የሚደረጉ ምርምሮች ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር የሰው፣ የአካባቢ እና የእንስሳትን ጤና ለማስጠበቅ ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ። በጥናታዊ ጽሁፋቸው የአፈር እርጥበትን ማስጠበቅ፣ አሲዳማነትን መቀነስ፣ ምርታማነትን መጨመርና ካርቦንን አምቆ የመያዝ አቅምን ማሳደግ ላይ ያተኮረ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም የተለያዩ ጥናቶች መስራታቸውን ጠቁመው ይህም መንግስት ዘርፉን ለማሻሻል የጀመረውን ውጥን የሚደግፍ በመሆኑ ወደ አርሶ አደሮች በማምጣት እንደሚተገበርም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የተፈጥሮ ሀብት አያያዝና የአየር ንብረጥ ለውጥ መቋቋም ፕሮግራም ዳይሬክተር አወቀ ሙሉዓለም(ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋማቸው የሀገሪቱን ግብርና ለማሻገር በጥናት የተደገፈ ስራ በመስራት የግብርናን ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ መንግስት በዘርፉ የያዘውን ውጥን ለማሳካት እየተጋ መሆኑን በመጥቀስ ለስራው ውጤታማነት ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ይህም አርሶ አደሩ ከቤተሰብ ፍጆታ ያለፈ ትርፍ ምርት በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ገበያን በማረጋጋት በኩል አበርክቶ እንዲኖረው ትልቅ ድርሻ መወጣቱን አመልክተዋል። በመድረኩ ከ10 በላይ ጥናታዊ ጽሁፎች የቀረቡ ሲሆን ሙያዊ ውይይት ተደርጎ የፖሊሲ አቅጣጫ የማመላከት ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል።
በምርምር ስራዎች የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚደረገው ጥረት ይጠናከራል
Apr 4, 2026 304
ሰመራ፣መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ) ፡-በምርምር ስራዎች የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት ማጠናከር እንደሚገባ የሠመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ዓሊ ተናገሩ። በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ለዘጠነኛ ጊዜ የተዘጋጀ የአደጋ ተጋላጭ ማህበረሰብ ዝግጁነትና መቋቋም ላይ ያተኮረ ሲምፖዚየም በሰመራ ከተማ ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እንደተናገሩት፤ የምርምር ስራዎችን በማጠናከርና ተግባራዊ በማድረግ የአደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት መደገፍ ይገባል። የምርምር ውጤቶቹ ማህበረሰቡን ከማንቃትና ተጋላጭ እንዳይሆኑ ከማድረግ አኳያ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል። በተለይም ተመራማሪዎች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት የአካባቢውን ችግር ተረድተው እገዛ ሊያደርጉ እንደሚገባ አመልክተው በአካባቢው የሚገነቡ ህንፃዎች ጭምር ግምት ውስጥ ሊገቡ እንደሚገባም አመልክተዋል። በሲምፖዚየሙ ላይ የተገኙት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመሬት መንቀጥቀጥ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አታላይ አየለ በበኩላቸው፤ የተፈጥሮ አደጋዎች ከመከሰታቸው በፊት ዝግጅት ማድረጉ የጉዳት መጠኑን ለመቀነስ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ውሳኔ ሰጪ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ማድረግ፣ ፖሊሲዎችን ማጤንና የህንፃ ግንባታ ደረጃ ግልፅ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። መገናኛ ብዙሃን ጉዳዩን አስመልክተው እያከናወኑ ያለው የግንዛቤ ማስጨበጥ ተግባር ሊጠናከር እንደሚገባ ጠቁመው የምርምር ግኝቶችን በየጊዜው በማውጣት ለሚመለከታቸው አካላት ማጋራት ይገባል ብለዋል። በመድረኩም ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ተመራማሪዎች፣ የትምህርት ሚኒስቴርና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያ በያዝነው ዓመት መድኃኒት የማምረት አቅሟን ከ50 በመቶ በላይ ታደርሳለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Apr 4, 2026 124
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ መድኃኒት የማምረት አቅሟን፣ በ2018 ዓ.ም ከ50 እስከ 55 በመቶ ለማድረስ ማቀዷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከልን ዛሬ መርቀው ከፍተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በአንድ ሀገር ጉዞ ውስጥ የሚያጋጥሙ ችግሮችንና ፈተናዎችን ወደ መልካም ዕድል መቀየር እጅጉን አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በተከሰተበት ወቅት፣ አፍሪካ ለከፍተኛ አደጋ ትጋለጣለች የሚል ግምት በበለጸጉት ሀገራት በኩል የነበረ ቢሆንም፣ ያ ሳይሆን መቅረቱን አመልክተዋል። ይሁን እንጂ ወረርሽኙ በሽታን አስቀድሞ የመከላከል ዝግጁነት ምን ያህል እንደሚያስፈልግ ትልቅ ትምህርት ሰጥቶ ማለፉን ተናግረዋል። በወቅቱ መንግስት በምግብ፣ በልብስ እና በመድኃኒት ዘርፎች ራስን መቻል አለብን የሚል ግልጽ አቅጣጫ ይዞ ወደ ሥራ መግባቱን አስታውሰዋል። በዚህም በምግቡ ዘርፍ ስንዴን ጨምሮ ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፣ በመድኃኒት በኩል ግን በሚፈለገው ደረጃ ለውጥ አለመታየቱን ጠቁመዋል። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ኢትዮጵያ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ ማምረት የምትችለው መድኃኒት ስምንት በመቶ ብቻ እንደነበርም አስታውሰዋል። በቂ የመድኃኒት ምርት ማምረት አለመቻሉ፣ ሻጮች የግዢ መድኃኒት መያዛቸውና የግሉ ዘርፍ በምርት ሂደቱ ላይ ለመሳተፍ እምብዛም ፍላጎት አለማሳየቱ በመንግስት በኩል ትልቅ ቁጭት እንዲፈጠር አድርጓል ብለዋል። በምግብ፣ በልብስና በመድኃኒት ራሱን ያልቻለ ሀገር የተሟላ ሉዓላዊነት እንደሌለው ጠቅሰው፣ ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገባት የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ማስገኘታቸውን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ ማምረት የምትችለው የመድኃኒት ድርሻ ቀደም ሲል ከነበረበት ስምንት በመቶ አሁን ላይ ወደ 44 በመቶ ከፍ ማለቱን ገልጸዋል። በቅርብ ጊዜያት የሚመረቁ ፋብሪካዎችን ታሳቢ በማድረግም በተያዘው ዓመት የማምረት አቅሙ ከ50 እስከ 55 በመቶ እንደሚደርስም አስታውቀዋል። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ ቢያንስ መድኃኒትና ክትባትን በራሷ አቅም እንድታመርት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። በአንጋፋው የአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም የተመረቀው ዘመናዊ የምርምር ማዕከል ከፍተኛ ወጪ የወጣበት መሆኑን ጠቁመው፣ ለማዕከሉ ለመድኃኒትና ክትባት ምርት መሠረት የሚጥሉ ዕውቀቶችን መያዙንም አመልክተዋል። በኮቪድ ወቅት የናሙና ምርመራ ወደ ደቡብ አፍሪካ ይላክ እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አዲሱ የምርምር ማዕከል እንዲህ ያሉ ምርመራዎችን እዚሁ የማከናወን አቅም እንዳለው ገልጸዋል። ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስና ባዮኢንፎርማቲክስ ክፍሎችን እንዲሁም የመድኃኒቶችን ጥራት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ ማዕከልን ያካተተ ሲሆን፤ ለድንገተኛ የጤና አደጋዎች ምላሽ የመስጠት አቅምን በመገንባት ረገድም እንደ ዋልታ የሚያገለግል መሆኑን አመልክተዋል። ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር ረገድ ማዕከሉ በመድኃኒት ምርት ራስን ለመቻልና ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። በጥረትና በትጋት ከሰራን ሀገርን ማሳደግና ማበልጸግ እንደሚቻል ይህ ማዕከል ትልቅ ማሳያ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየተደረገ ባለው ጥረት አበረታች ውጤት እየተገኘ ነው
Apr 4, 2026 98
ደሴ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየተደረገ ባለው ጥረት አበረታች ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) አስታወቁ። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከወሎ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፖሊሲ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እና በስታርታፕ ፖሊሲ አዋጅ ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሂዷል። ሚኒስትሩ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን በማድረግ ሁለንተናዊ እድገትን ለማፋጠን በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። ባለፉት ዓመታት ለዚህ አጋዥ የሆኑ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና መመሪያዎችን በማዘጋጀት ወደ ሥራ መገባቱ "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" እቅድን በስኬት ለማጠናቀቅ ማስቻሉን አውስተዋል። በተለይም በሪፎርም ማሻሻያዎችና በተቋማት ግንባታ፣ በመሠረተ ልማትና በሰው ኃይል ልማት፣ በኢንተርኔት ተደራሽነትና በዲጂታል ክፍያ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። የተገኘውን ተሞክሮ በማስፋት "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂን በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)፣ በጤና፣ በግብርና እና በሌሎች ቁልፍ ዘርፎች ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቶችን በማበረታታትና ወደ ተግባር እንዲገቡ በማድረግ፣ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ መሪ እንድትሆን ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል። ለዚህ ውጤታማነትም ሚኒስቴሩ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን ጠቁመው፣ የዛሬው መድረክም የተጀመሩ ተግባራትን ማጠናከር የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አወል ሰይድ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ዩኒቨርሲቲው የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲውን የውስጥ አሠራር በቴክኖሎጂ ከመደገፍ ባለፈ፣ የሌሎች ተቋማትን አቅም በመገንባት የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ እንዲሳካ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ካሳ ሻውል(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ የሀገር እድገት መሠረት በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎታል ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶችን በማሟላት አገልግሎቱን ማዘመን መቻሉንና ሂደቱን በጥናትና ምርምር እያገዙ እንደሚገኙም ገልጸዋል። በመድረኩ ከወሎ፣ ከመቅደላ አምባ፣ ከወልድያ፣ ከራያ እና ከሰመራ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም ከፌዴራል ተቋማት የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ስፖርት
ነጌሌ አርሲ አዳማ ከተማን አሸንፏል
Apr 5, 2026 52
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡- በ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት ነጌሌ አርሲ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 ረትቷል። 9 ሠዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ፤ ሁለቱም እስከ እረፍት ድረስ ያለምንም ግብ አቻ ሆነው ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል። ከእረፍት መልስ ዳዊት ተፈራ እና ሮሆቦት ሰላሎ ለነጌሌ አርሲ እንዲሁም ዳዋ ሁቴሳ ለአዳማ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ውጤቱን ተከትሎም ነጌሌ አርሲ በ41 ነጥብ 3ኛ እንዲሁም አዳማ ከተማ በ33 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ውድድሩ ህብረ ብሄራዊ አንድነትና ሀገራዊ መስተጋብርን በአንድ መድረክ ያሳየ ነው
Apr 5, 2026 86
ሐረር፤መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የባህልና ስፖርቶች ውድድር ህብረ ብሄራዊ አንድነትና ሀገራዊ መስተጋብርን በአንድ መድረክ ያሳየ መሆኑን የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ህይወት መሀመድ ገለጹ፡፡ "የባህል ስፖርቶች ልማት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 20 እስከ 27 በሐረሪ ክልል ሲካሄድ የነበረው 23ኛው የኢትዮጵያ የባህልና ስፖርቶች ውድድር እና 19ኛው የባህል ፌስቲቫል ተጠናቋል። በውድድሩም በባህል ስፖርት ውድድር የኦሮሚያ ክልል አጠቃላይ አሸናፊ ሲሆን አማራ ክልልና አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 2ኛ እና 3ኛ ሆነዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በባህል ፌስቲቫል በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ ኦሮሚያና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች 2ኛ እና 3ኛ ሆነዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበኩሉ የስፖርታዊ ጨዋነት ዋንጫ ተሸላሚ መሆን ችሏል። በመርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ህይወት መሀመድ፡ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የባህልና ስፖርቶች ውድድር ህብረ ብሄራዊ አንድነትና ሀገራዊ መስተጋብርን በአንድ መድረክ ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። የሐረሪ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙራድ አብዲ በበኩላቸው፤ በክልሉ የባህል ስፖርት እና ፌስታቫል መዘጋጀቱ መነቃቃትን ፈጥሯል ብለዋል። መርሃ ግብሩ ከስፖርት መድረክነት ባለፈ የህዝቦች ትስስርን በማጠናከርና መሠረተ ልማቶችን ማስተዋወቅ ያስቻለ መሆኑንም ገልጸዋል። አሸናፊ የነበሩ ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ከእለቱ የክብር እንግዳና በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳና የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት ወይዘሮ ህይወት መሀመድ እጅ የተዘጋጀላቸውን የዋንጫ ሽልማት ተረክበዋል። 24ኛውን የባህል ስፖርቶች ውድድር እና የባህል ስፖርት ፌስቲቫልን የሲዳማ ክልል እንዲያሰናዳ መመረጡም ይፋ ተደርጓል።
በተጠባቂው መርሐ ግብር ባርሴሎና አትሌቲኮ ማድሪድን በመርታት በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል
Apr 4, 2026 369
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በስፔን ላሊጋ የ30ኛ ሳምንት ተጠባቂ ጨዋታ ባርሴሎና አትሌቲኮ ማድሪድን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በዋንዳ ሜትሮፖሊታኖ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጁሊያኖ ሲሞኒ በ39ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል መሪ መሆን ችሏል። ማርከስ ራሽፎርድ በ42ኛው ደቂቃ ባሳረፈው ግብ ባርሴሎና አቻ ሆኗል። ተቀይሮ የገባው ሮበርት ሌዋንዶውስኪ በ87ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ጎል ለባርሴሎና ወሳኝ ሶስት ነጥብ አስገኝቷል። የአትሌቲኮ ማድሪዱ ኒኮላስ ጎንዛሌዝ በመጀመሪያው አጋማሽ ማብቂያ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። የባርሴሎናው ጄራርድ ማርቲን ሁለተኛው አጋማሽ በተጀመረ 46ኛው ደቂቃ ቀይ ካርድ ቢመለከትም በቪዲዮ በታገዘ ዳኝነት ታይቶ የመጀመሪያ ውሳኔ ተሽሮ ወደ ቢጫ ካርድ ተቀይሯል። የቀይ ካርዱ መሻር የአትሌቲኮ ማድሪድ የቡድን አባላት እና ደጋፊዎችን ያስቆጣ ሲሆን ማርቲን በሰራው ጥፋት በቀይ ካርድ ሜዳ መውጣት ነበረበት በሚል ቅሬታቸውን አሰምተዋል። ባርሴሎና ያገኘውን የቁጥር ብልጫ ተጠቅሞ በፈጠረው ጫና ግብ አስቆጥሯል። ጨዋታው ጉልበት የተቀላቀለበት መሆኑ በርካታ ቢጫ ካርዶች እንዲመዘዙ አድርጓል። ውጤቱን ተከትሎ ባርሴሎና ነጥቡን ወደ 76 ከፍ በማድረግ መሪነቱን አጠናክሯል። በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። ከተከታዩ ሪያል ማድሪድ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ከፍ አድርጓል። ባርሴሎና በሊጉ 25ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በሊጉ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አትሌቲኮ ማድሪድ በ57 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ሪያል ማድሪድ ዛሬ ባደረገው ጨዋታ በሪያል ማዮርካ ባልተጠበቀ ሁኔታ የ2 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል። ባርሴሎና እና አትሌቲኮ ማድሪድ ረቡዕ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሚያደርጉት የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ ጨዋታ ይጠበቃል።
አርሰናል ከኤፍኤ ካፕ ውድድር ውጪ ሆነ
Apr 4, 2026 230
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በኤፍኤ ካፕ ሶስተኛ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ሳውዝሃምፕተን አርሰናልን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በሴንት ሜሪ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሮስ ስቲዋርት እና ሼ ቻርልስ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ቻርልስ በ85ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፈው ጎል ሳውዝሃምፕተን አሸናፊ አድርጓል። ለአርሰናል ቪክቶር ዮኮሬስ ብቸኛውን ግብ አስቆጥሯል። በጨዋታው አርሰናል ብልጫ ወስዶ ቢጫወትም ተጨማሪ ጎል ማስቆጠር አልቻለም። ተጋጣሚው ሳውዝሃምፕተን ያገኛቸውን የግብ እድሎች በሚገባ ተጠቅሟል። ውጤቱን ተከትሎ 14 ጊዜ ዋንጫውን በማንሳት ስኬታማ የሆነው አርሰናል በሩብ ፍጻሜው ተሰናብቷል። ለአራት ዋንጫዎች ሲፎካከር የነበረው አርሰናል የሚፎካከርባቸው ዋንጫዎች ብዛት ወደ ሁለት ዝቅ ብለዋል። በእንግሊዝ ሁለተኛ ዲቪዚዮን (ሻምፒዮንሺፕ) የሚገኘው ሳውዝሃምፕተን ሳይጠበቅ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አልፏል። ዛሬ በተደረጉ ሌሎች የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ማንችስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 4 ለ 0፣ ቼልሲ ፖርት ቫሌን 7 ለ 0 በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜ አልፈዋል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ ከካርበን ግብይት መስፈርቶች ጋር የሚጣጣሙ የደን አያያዝ ስራዎችን እያከናወነች ነው
Apr 4, 2026 137
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የካርበን ግብይት መስፈርቶች ጋር የሚጣጣሙ ዘላቂ የመሬትና የደን አስተዳደር ልምዶችን እያሳደገች መሆኑን የአረንጓዴ አሻራ የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) ገለጹ። ዶክተር አደፍርስ ወርቁ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የካርበን ክምችት መኖሩን በማንሳት፤ አብላጫው በደን ሀብት ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ ሀገሪቱ ከካርበን ሽያጭ የምታገኘው ገቢ እንዲጨምር የጎላ ሚና እየተጫዎተ እንዳለ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በርካታ የብዝሃ ህይወት ባለቤት በመሆኗ የተሻለ የካርበን ክምችት ለመያዝ የሚያስችል ተስማሚ ሥነ-ምህዳር እንዳላት ዶክተር አደፍርስ ገልጸዋል። ሀገሪቱ በአየር ንብረትና በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈች መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ካርበንን ከአየር ላይ በማስወገድ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ መንገድ እንዲከማች እያደረገ ነው ብለዋል። ቀደም ሲል በደን መመንጠርና ባልተገባ የመሬት አያያዝ ምክንያት ወደ ህዋ ይለቀቅ የነበረውን ሙቀት አማቂ ጋዝ መከላከል የሚያስችሉ ተግባራት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካይነት እየተተገበሩ እንዳለ አስረድተዋል። በዚህም ከካርበን ግብይት መስፈርቶች ጋር የሚጣጣሙ ዘላቂ የመሬት እና የደን አሥተዳደር ልምዶችን ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልጸዋል። ሁለተኛው ደግሞ እጽዋት በሚተከሉበት ወቅት ቀደም ሲል ወደ ህዋ የሄደውን ካርበን አምቀው የሚመልሱበትን አሰራር ተግባራዊ በማድረግ እና ከልቀት የተጠበቀውን ካርበን ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እያከናወነች ባለችው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት የካርበን ሽያጭን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑንና ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር የግዢ ውል ስምምነት እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም የኖርዌይ መንግስት እንደመነሻ የ75 ሚሊዮን ዶላር የካርበን ግዢ እንዲሁም የዓለም ባንክም እንዲሁ የግዢ ውል ማሰሩን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ኖርዌይ እና የዓለም ባንክ ሊገዙት ከሚፈልጉት በላይ ካርበን ማመንጨቷን ጠቁመው፤ እስከ አንድ ቢሊየን ዶላር ሊያመጣ የሚችል ካርበን ሀብት መኖሩን ገልጸዋል። በዓለም ገበያ ላይ ለካርበን ግዢ የሚመደበውን ከፍተኛ ሀብት ወደ ኢትዮጵያ የካርበን ሽያጭ ማምጣት የሚያስችሉ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። በዓለም ላይ ያለውን የካርበን ፋይናንስ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከማጠናከር ባለፈ ሰነዶች የማደራጀትና ሌሎች ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ለዲጂታልና ታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ ነው
Apr 3, 2026 375
አዳማ ፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም ዘመናዊ የቴሌኮም አገልግሎትን ከማስፋት ባሻገር ለዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ኢትዮ ቴሌኮም በአዳማ ከተማ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከል በመገንባት በዛሬው እለት አገልግሎት አስጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ በኢትዮጵያ የዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአዳማ ከተማ ተገንብቶ በዛሬው እለት ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከልም የዚሁ ልማት ጥረት አካል መሆኑን ጠቁመዋል። የአዳማው ማእከል በአንድ ጊዜ 12 ተሽከርካሪዎችን ቻርጅ የሚያደርግ አቅም እንዳለው ተናግረው በሌሎች አካባቢዎችም የማስፋት እቅድ መኖሩን ገልጸዋል። ኢትዮ ቴሌኮም ከፈጣንና ዘመናዊ የቴሌኮም አገልግሎት በተጨማሪ ለዲጂታልና የታዳሽ ሃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም መሰረት አዲስ አበባን ጨምሮ በክልል ከተሞች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጀ ማድረጊያ ማዕከላትን በማስፋፋት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ፤ የስማርት አዳማ ፕሮጀክት ተቀርፆ አሰራርና አገልግሎቶችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ሂደት የኢትዮ ቴሌኮም አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አንስተው በከተማዋ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ማዕከል ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል።
በመጪው ሚያዚያ ወር በአብዛኞቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተሻለ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ይኖራል
Apr 3, 2026 83
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ በመጪው ሚያዚያ ወር በአብዛኞቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጠንና ሥርጭት የተሻለ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፤ ከመጋቢት 23 እስከ ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም የበልግ ዝናብ በመጠንና ስርጭት ከፍተኛ ድርሻ የሚወስድበት ወቅት መሆኑን ገልጿል። በዚህም በመጪው ሚያዚያ ወር በአብዛኛዎቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ከቀደሙት ሁለት የበልግ ወራት በመጠንና ሥርጭት የተሻለ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ እንደሚኖር አስታውቋል። ይህም የአየር ጠባይ ሁኔታ የበልግ አብቃይና ተጠቃሚ አካባቢዎች ለሚያከናውኑት የግብርና ሥራ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር ይጠበቃል ብሏል ኢንስቲትዩቱ በመግለጫው። በተለይም በተያዘው የመጋቢት ወር የሚስተዋለው ተከታታይ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ በቡቃያና በተለያየ የዕድገት ደረጃ ላይ ለሚገኙ የበልግ ሰብሎች ምርታማነት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጿል። በደቡብና ደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ የሚጠበቀው እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ለቦረና፣ ጉጂና መሰል ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች ሰብል ልማት፣ ግጦሽ መሬትና የውሃ አቅርቦት ወሳኝ መሆኑንም አመላክቷል። በዚህም የበልግ አብቃይ አካባቢ አርሶና አርብቶ አደሮች ማሳቸውን በማዘጋጀት የሚጠበቀውን አመቺ እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ለመጠቀም ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ አሳስቧል። በበልግ ዝናብ መዋዠቅ አዝማሚያ ምክንያት ዝናብ አጠር የሆኑ አካባቢዎች የሚያጋጥማቸውን ተከታታይ ደረቃማ ሁኔታ ለመቋቋም እርጥበትን በማሳ ማቆየት የሚያስችል ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ኢንስቲትዩቱ አስውገንዝቧል። በሌላ በኩል በአንዳንድ አካባቢዎች በሚኖር ከባድ ዝናብ ሊፈጠር ከሚችል የመሬት መንሸራተት፣ የአፈር መሸርሸርና ቅፅበታዊ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭነት ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስቧል።
የክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዜጎችን ተጠቃሚነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው
Apr 3, 2026 91
ባህር ዳር፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በለውጡ ዓመታት የተተገበረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዜጎችን ተጠቃሚነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከእለት ወደ እለት ስኬታማ እየሆነ መምጣቱ እየተመሰከረለት ነው። በመርሃ ግብሩ በብዛትና እና በአይነት መጠነ ሰፊ ችግኞች ተከላ መካሄዱን ለአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፤ ለደን ሽፋን መጨመር ብሎም የምግብ ዋስትን ለማረጋገጥ እያስቻለ ነው። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ መሰሉ ብርሃኑ ለኢዜአ እንዳሉት፤በለውጡ ዓመታት የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዘርፉን ልማት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው። መርሃ ግብሩ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ለውጥ መሻሻል፤ ለደን ሽፋን መጨመር እና የምግብ ዋስትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ መሆኑንም አስረድተዋል። መርሃ ግብሩ ተግባራዊ መደረጉ በክልሉ 13 ነጥብ 9 በመቶ የነበረውን የደን ሽፋን ወደ 18 ነጥብ 9 በመቶ ለማስደግ እንደተቻለም ነው የተናገሩት። በነዚሁ የለውጥ አመታት በ22 ሺህ 189 ተፋሰሶች ላይ በተካሔደው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ምርታማነት ለማሳደግ ያስቻለ መሆኑንም አብራርተዋል። የአረንጓደ ልማቱ በተለይም ለንብ ማነብ፣ ለእንስሳት እርባታና ለፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አንስተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 215
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 529
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት። ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው
Mar 22, 2026 218
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
የኢጋድ እና ጃፓን ትብብር መጠናከር ለቀጣናዊ ሰላም የጎላ ሚና አለው
Mar 9, 2026 320
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ጃፓን በቀጣናው ሰላም ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሠሩ ገለጹ። የኢጋድ ምክትል ዋና ፀሐፊ መሐመድ አብዲ ዋሬ ከጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ዳይሬክተር ሂሮኒሪ ሱዙኪ ጋር በጅቡቲ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በኢጋድ ቀጣና ስላለው የሰላም እና ደኅንነት ሁኔታ ሐሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቀጣይም ትብብራቸውን በይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሠሩ ማረጋገጣቸውን ኢጋድ ሴክሬተሪያት መረጃ ጠቁሟል። ጃፓን ለኢጋድ እና አባል ሀገራት፤ በቀጣናው ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት መረጋገጥ ሥራ ዋና አጋር ሆና መቀጠሏም ተመላክቷል።
ሐተታዎች
የጤና ነገር ...
Apr 3, 2026 2033
በዮሐንስ ደርበው የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። የኒውትሬሽን ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ የሰው ልጅ የሰውነት ክፍል 60 በመቶው ውኃ እንደመሆኑ ለተስተካከለ ጤና ሚዛን መጠበቅ በቂ ውኃ መጠጣት ይገባል። ውኃን በትክክለኛው መጠንና ጊዜ መውሰድ ከተቻለ የኩላሊት ህመም ተጋላጭነትን 50 በመቶ መቀነስ እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ነገር ግን ሰውነት የሚፈልገውን የውኃ መጠን በአግባቡ ካላገኘ ለዕለታዊ እና በጊዜ ሂደት ሥር ለሚሰድዱ ህመሞች የመጋለጥ ዕድል እንደሚጨምርም ያነሳሉ። ለመሆኑ ሰውነት የሚፈልገውና በቂ የውኃ መጠን የሚባለው መጠኑ ስንት ነው? በቂ ውኃ አለመጠጣትስ የሚያስከትለው ችግር ምንድን ነው? በሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎች ላይ የኒውትሬሽን መምህር፣ ተመራማሪ እና ደራሲ ይሁኔ አየለ ምላሽ አላቸው። አንድ ሰው የሚያስፈልገው የውኃ መጠን በዕድሜ፣ ጾታ፣ በሥራ ባሕርይ፣ በመኖርያ አካባቢ፣ እንደ ጤና ሁኔታው እና እንደ ሰውነት ክብደቱ እንደሚወሰንም በምላሻቸው አስገንዝበዋል። ለምሳሌ የስኳር ታማሚዎች፣ የምታጠባ እናት፣ በዕድሜ የገፉ ሰዎች፣ ብዙ አድካሚና ላብ የሚያወጡ፣ በሞቃታማ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች በቀን 3 ሊትር ውኃ መጠጣት አለባቸው ይላሉ። በአማካይ ግን በቀን አንድ ሰው ከ2 እስከ 3 ሊትር ውኃ መጠጣት እንደሚጠበቅበት ይገልጻሉ። ጤናማ ሕይወት የሚመሠረተው ከውኃ ነው፤ ለምሳሌ ውኃማውን 60 በመቶ የሰውነት ክፍል ሚዛን ለማስጠበቅ የግድ አስፈላጊውን መጠን ውኃ መጠጣት እንደሚገባ ይመክራሉ። በሰውነት ውስጥ የሚካሄደው ሕይወታዊ ሂደት (ባዮሎጂካል ፕሮሰስ) ውኃን መሠረት ያደረገ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለምሳሌ ለተስተካከለ የሥርዓተ-ምግብ ሂደት፣ ቆሻሻን ከሰውነት አጣርቶ ለማስወጣት፣ የአጥንት መገጣጠሚያ ሥራን ለማስተካከል እና ለሌሎችም በርካታ የሰውነት ክፍሎች የተሳለጠ ተግባር ውኃ ቁልፍ መሆኑን አንስተዋል። ይህን ተከትሎም ውኃ ካሎሪ አልባው መድኃኒት (ተፈጥሯዊው መድኃኒት) እስከመባል መድረሱን ነው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ያስረዱት። ሰውነት የሚያስፈልገውን ያህል ውኃ አለመጠጣት ግን ድካም ያስከትላል፤ ለማየት፣ ለመንቀሳቀስ፣ ለመሥራት፣ ለማሰብ፣ ለመረጋጋት . . . አያስችልምና ሲሉ ያብራራሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንድ ሰው ውኃ የመጠማት መጠኑ ከአራት በመቶ በላይ ከሆነ ለሞት ሊጋለጥ እንደሚችልም ጠቅሰዋል። ውኃ አለመጠጣት፤ የጨጓራ ህመምን በማባባስ ማስገሳት፣ የቆዳ ድርቀትና ግርጣት፣ የኩላሊት ህመም ሌሎች የሰውነት ክፍሎችም ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሠሩ ያደርጋል ነው ያሉት። ከምግብ በፊት 30 ደቂቃ ቀድሞ ውኃ መጠጣት ውፍረትን ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በቂ ውኃ ከመጠጣት በተጨማሪ ፍራፍሬዎችንና አትክልቶችን ማዘውተር እንደሚመከርም ገልጸዋል። የፈላ ውኃ እና የዝናብ ውኃን በብዛት መጠጣት በሰውነት ውስጥ ያሉ ንጥረ ነገሮችን በማስወገድና በኩላሊት ላይም ጫና እንደሚፈጥር አመላክተዋል። ለተስተካከለ ጤናማ ሕይወት የግድ ውኃ መጠጣትን ልማድ ማድረግ እንደሚገባም ይመክራሉ። #ውኃ_መጠጣት #ጤና #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency
ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች
Apr 3, 2026 2009
በዮሐንስ ደርበው የለውጡ መንግሥት ኢትዮጵያን ማሥተዳደር ከጀመረ እነሆ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ላይ 8 ዓመት ሞላው። በእነዚህ ዓመታት በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚው፣ በማኅበራዊ ዘርፉ በዲፕሎማሲውና በሌሎችም መስኮች የተለያዩ ስኬቶች ተከናውነዋል። በእነዚህ ጥቂት ዓመታትም ለማሳካት ቀርቶ ለማሳብ የማይደፈሩ ብዙ ውጤቶችም ተመዝግበዋል። የተገኙት ስኬቶች ከጊዜያቸው የፈጠኑ ናቸው። ለዚህም ሕዝቡ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በነቂስ እየወጣ አድናቆቱን ገልጿል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሰጡት የሰላ አመራርነትና ቁርጠኝነትም አክብሮቱንና ምሥጋናውን ገልጿል። የለውጡ መንግሥት አካሄድ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የልማት ፕሮጀክቶችም በይበልጥ ተስፋፍተውና ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መንግሥት ለሚያደርገው ጥረት ከጎኑ እንደሚቆሙም በድጋፍ ሰልፍ ላይ ባስተጋቧቸው መልዕክቶቻቸው አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ በለውጡ መንግሥት ለማሳካት ቀርቶ ለማሰብ የማይደፈሩ ተግባራት ተከናውነዋል። ከእነዚህ ከፍተኛ ጥቅም ከተገኘባቸው የታሪክ እጥፋትን ካሠረጹ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል ጥቂቶቹን ቀጥለን በወፍ በረር እንዳሥሣለን። ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ሥልጣኔ - በምርጫ ካርድ መምረጥ የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። • የኮሪደር ልማት እንደምናውቀው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነትና ልዩ ትኩረት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከሁሉም አስቀድሞ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ ነው። አሁን ላይ ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የበርካታ ከተሞችን ገጽታ የቀየሩ አስደማሚ ሥራዎች ተከናውነውበታል። ይህም በገጠር ጭምር ተጠናክሮ የቀጠለ ጉዳይ ነው። ለዘመናት አሮጌ ገጽታዋን ይዛ ያሸለበችውን አዲስ አበባ እንደ አዲስ የፈጠራትም ይኸው ፕሮጀክት ነው። አሁን ላይ መዲናይቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን ለውጥ ዐይተው ዝም ማለት አልቻሉም። ከመደመማቸው አንጻር የዘወትር አጀንዳቸውም እያደረጓት ይገኛሉ። ይህንን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት፤ ኮሪደር ልማት ማለት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት ነው ማለታቸው ይታወሳል። ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑንንም አስረድተዋል። ከለውጡ መንግሥት ዐበይት የትኩረት መስኮች አንዱ የሆነውን የቱሪዝም ዘርፉን እንቅስቃሴ ለማሳደግም ቁልፍ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ ድርብርብ ፕሮጀክት ነው የኮሪደር ልማት። • የበጋ መስኖ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የለውጡ መንግሥት ዋነኛ ትኩረቱ ነው። ለዚህም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አንዱ ማሳኪያ ሥልት አድርጎ እየተጋ ይገኛል። የበጋ መስኖ ስንዴ ኢትዮጵያ ስንዴን ከውጭ ማስገባት አቁማ መላክ እንድትጀምር ያስቻለ ኢኒሼቲቭ ነው። በዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችና በሜካናይዜሽን ታግዞ በስፋት እየተሠራበትም ይገኛል። ከለውጡ መንግሥት ወዲህ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ምክንያት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በምርታማነት ማደግና የሥራ ዕድል በመፍጠር አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብም ከፍተኛ ውጤት ተገኝቶበታል። ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ ስንዴ ላይ ባሳየችው ትጋት፤ ፍጆታዋን በራሷ ዐቅም የሸፈነችው፣ ስንዴን ከውጭ ማስገባትን ያቆመችው፤ ስንዴን ወደ ውጭ መላክ የጀመረችው በለውጡ መንግሥት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ በመሸለም ለጥረታቸው ዕውቅና መስጠቱም ይታወሳል። • መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀደም ሲል አንድ ጉዳይን ለማስፈጸም እዚያም እዚህም መንከራተት የግድ ነበር። በዚህ አያበቃምና ወረፋውም ሌላ ችግር ነው። መንግሥት በተለያዩ መድረኮች ባካሄዳቸው ሕዝባዊ ውይይቶች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉልን የሚሉ እሮሮዎች በረከቱ። መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል ሥራ ወደ ተግባር አሥገባ። በዚህም መሠረት ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ ጀመረ። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነውም አሉ። ለዚህ ቁርጠኝነታችን አንዱ ማሳያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመራቸውንም ገለጹ። እንግዲህ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ አንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ ታግዘው በተሳለጠ ሂደት እንዲሰጡ በማድረግ የተገልጋይን እንግልት፣ ገንዘብ እና ጊዜ መቀነስ ያስቻለ አሠራር ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት ተደርጎም ይወሰዳል። በየከተሞቹም እየተስፋፋ ነው። • አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ አይ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ተጠቃሚ እንድትሆን ከፍተኛ ጉጉት እንዳላቸው በቁጭት በተለያዩ መድረኮች ያነሳሉ። ለዚህም መፍትሔ ዘይደው ተቋማትን ከማቋቋም ጀምሮ ለዘርፉ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ ተግተዋል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂው ጋር አብሮ ለመጓዝ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን አቋቋመች። የኤ አይ ዩኒቨርሲቲ በመክፈት በግብርናው፣ በጤናው እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠርም በሂደት ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት ቀይሮ ወደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ሕንፃ በተዛወረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአምስት ዓመት ውስጥ አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ መድረሱ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ የሮቦቶችን ሶፍትዌር ብቻ ሳይሆን ውጫዊ የአካል ክፍልን (ሃርድዌር) መሥራት ጀምሯል ብለዋል። ድሮን ማምረት ብቻ ሳይሆን የማነጋገር ዐቅም እየፈጠረ ያለ ተቋም መሆኑንም አንስተዋል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ደረጃ የሚወዳደር አሠራርን የሚከተል መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ምርቶችን አውጥቷል ማለታቸው ይታወቃል። ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮሉሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን ሲሉ ማስገንዘባቸውም ይታወሳል። • የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው። በዚህ ሂደት ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊታአውራሪነት ይጠቀሳል። በተደራጀና ተቋማዊ ሆኖ ባልተቆራረጠ አካሄድ እየተከናወነ ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተተከሉ ችግኞችም በየዘርፉ ተጠቃሚነት አድጓል፤ ተጠናክሮም ይቀጥላል። • የሌማት ትሩፋት ከመጋቢት ሥጦታዎች አንዱ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ነው። የምርት አቅርቦትን በማስፋት ለተረጋጋ ግብይት እና ለተመጣጠነ ሥርዓተ-ምግብ ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከት ላይም ይገኛል። ኢኒሼቲቩ ለግብርና ኢንቨስትመንትና ለሀገራዊ የሥርዓተ-ምግብ መሻሻል ጉልኅ ሚና እየተጫወተ ነው። የዋጋ ንረትን በማረጋጋት፣ የምርት ስብጥርን በማሳደግና በዘላቂነት በማቅረብ ረገድም የጎላ ሚና አለው። የግድ ሰፋፊ መሬት መፈለግ ሳያሻ በትንሽ ቦታ ብዙ በማምረት ፍጆታን ከመሸፈን አልፎ ኢኮኖሚን በመደጎም እና የሥራ ዕድል በመፍጠርም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው። • የቱሪስት መዳረሻ ልማት ቅርሶች እንዲጠገኑ፣ አዳዲስ ሎጂዎች እንዲገነቡ፣ በመዳረሻ ስፍራዎች መሠረተ-ልማት እንዲሟላ ያስቻሉ ተግባራት በለውጡ መንግሥት ተከናውነዋል፤ አሁንም ተጠናክሮ የቀጠለ እና ስኬታማ ኢኒሼቲቭ ነው። በዚህ ሂደት ከሐሳብ አመንጭነት ባሻገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የጻፉትን መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ ጭምር ለቅርስ ጥገናና ለቤተ-መጻሕፍት ግንባታ እንዲውል አድርገዋል። በተጨማሪም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት፤ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ ወደ ተግባር አስገብተዋል። በእነዚህ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። አማራጭ የቱሪስት መዳረሻም ሆነዋል። • የተቋማት ግንባታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል መሪል ሐሳብ በተካሄደው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ፤ የተቋማት ግንባታና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ብለዋል። በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ሲሉም አስገንዝበዋል በወቅቱ። ዘመን የማይለውጣቸው ዘላቂ ጠንካራ ሃገራዊ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ብዙ ርቀት መጓዝም ተችሏል። በመሆኑም የመንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲሆኑ በማድረግ እና ሥርዓት በተለዋወጠ ቁጥር የማይፈርሱ ወይም የሚሻገሩ ተቋማት መገንባት ተችሏል። ይህ ትጋት ተጠናክሮም ቀጥሏል።
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3636
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … በኢዜአ ዐይን …! የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 409
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 4, 2026 1070
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 20 እስከ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ስለ አዲስ አበባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ አዲስ አበባ ከዋና ከተማ በላይ መሆኗን ገልጸው፤ በፈጣን እንቅስቃሴ ላይ ያለች፣ ወደ ኢትዮጵያ ነገ የመግቢያ በር፣ በፍጥነት እየተለወጠች ያለች የሀገር የልብ ትርታ፣ ሁሉንም አሳታፊ እና አርቆ አሳቢ የሆነ የከተማ ልማት ትልማችን መገለጫ ናት ብለዋል። ፈጣን መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት፣ የዘመናዊ ከተማ መፍትሔዎችን በማቅረብ፣ አካታች በሆነ መልኩ መኖሪያ ቤት በመገንባት እና ዘላቂ ዕድገትን በማረጋገጥ እየሠራን ያለነው ዛሬን ብቻ ሳይሆን ለነገው ትውልድ ጭምር ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ የሚገኙ ከተሞቻችን ሰዎችን ለማብቃት፣ ዐቅምን ለመጠቀም እና ዘላቂ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ ቅርጽ ይዘዋልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። • አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መርቀው ከፍተዋል። በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው ብለዋል በወቅቱ። የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን እንዲሁም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከል ማከተቱን አብራርተዋል። ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። • የአዲስ ስፖርት ፓርክ መመረቅ ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የከተማችንን እድሳት ለማፋጠን እና የዜጎቻችንን ክብር ለመመለስ የገባነውን ቃል አንዱ ማረጋገጫ የሆነውን የአዲስ ስፖርት ፓርክን በይፋ መርቀን ከፍተናል ብለዋል። በ5 ነጥብ 7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ፕሮጀክት፤ በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ 15 አትሌቶችን የሚዘክሩ የክብር ሐውልቶችን በፓርኩ መሃል በማቆም፣ የጀግኖቻችን ታሪክ ለተተኪ ትውልድ ስፖርተኞች ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋልም ነው ያሉት። የኦሎምፒክ ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ኳስ፣ የቅርጫት ኳስና የሜዳ ቴኒስ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የ800 ሜትር የሩጫ ትራክን ጨምሮ፤ እያንዳንዱ የዚህ ማዕከል ክፍል የዓለም አቀፍ መስፈርቶችን እንዲያሟላ ተደርጎ ተገንብቷል ሲሉም ገልፀዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በአፋር ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፋር ክልል ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት በአዋሽ ወንዝ ተፋሰስ በመሥኖ እየለማ ያለው የሱፍ ምርት ለተሻገረ ግብርና እና ለተሻገረ ገጠር ራዕያችን ተደማሪ ሃብት ነው ብለዋል። በአፋር ክልል ያየነው በመሥኖ ተፋሰስ በረሃ የመሰለውን ምድር የምርት መትረፍረፊያ የማድረግ ትጋት፤ ለሌሎች በተለይም ከዓመት እስከ ዓመት ዝናብ አጠር አካባቢዎች ትልቅ የመማሪያ ሠነድ እንደሚሆን አመላክተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በተካሄደው "የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ቅንጅት ለሀገራዊ ሰላም እና ደኅንነት" በሚል መሪ ሐሳብ በተካሄደው ብሔራዊ የደኅንነት ኮንፈረንስ ላይ የተሳተፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የጸጥታና ደኅንነት ተቋሞቻችን ችግርን ወደ ዕድል እንዲቀየሩ ያስቻሉ ናቸው ብለዋል፡፡ ጉዟችን ተጀመረ እንጂ አልተቋጨምና ከትናንት ዕዳዎች ተላቀን፣ የዛሬ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን ለነገው ትውልድ የምትመጥን ሀገር ለመገንባት በዓላማ ጽናት እንቀጥላለን ሲሉም አመላክተዋል። • ስለ መጋቢት 24 መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ወደ ሥልጣን የመጣውን የለውጡን መንግሥት የሚደግፉ ሕዝባዊ ሰልፎች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተካሂደዋል። በእነዚህ ሰልፎች ላይም መንግሥት ባለፉት ሥምንት ዓመታት ያመጣቸውን ለውጦች እና የተገኙ ስኬቶችን የሚያወሱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) ለሰጡት ስኬታማ አመራርነት የሚያሞግሱና የሚያመሠግኑ መልዕክቶች ተስተጋብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ቀኑን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሕዝባዊ ግፊትና ትግል ያመጣው የመጋቢት ለውጥ ኢትዮጵያን ወደ ኋላ ያስቀሩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ስብራቶችን መጠገን ያስቻሉ ሪፎርሞች የተተገበሩበት ነው ብለዋል። ለሕዝባችን የላቀ ተጠቃሚነት፣ ለሀገራችን ክብርና ብልፅግና መሳካት አበክረን እንሠራለን ሲሉም ገልጸዋል። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በበኩሉ ቀኑን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በኃይልና በምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ አስደማሚ ስኬቶችን አስመዝግባለች ብሏል። የለውጡን መሠረት ከማስፋትና ከማጽናት ወደ ማላቅ የተሸጋገረችው ኢትዮጵያ፤ በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌትነቷን በተግባር ታውጃለች ሲልም ገልጿል። ይህን ለውጥ ዕውን ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ፤ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በድል እንደሚያሳርጉት ጥርጥር የለውም ነው ያለው። • የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ስምምነት የኢትዮጵያ መንግሥት በInvest in Ethiopia 2026 ፎረም፤ ከቻይና፣ ፖላንድ፣ ሕንድ፣ ሲንጋፖር እና ኬንያ ከመጡ አጋሮች ጋር የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ታሪካዊ የኢንቨስትመንት ስምምነት መፈራረሙን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት አስታውቋል። በታዳሽ ኃይል፣ በማዕድንና በአረንጓዴ አሞኒያ ዘርፎች ላይ ያተኮሩት እነዚህ ስምምነቶች፤ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችን ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ጉልህ ማሳያ ናቸው ብሏል። በተመሳሳይ ጽሕፈት ቤቱ ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለውን የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ የሚተካ የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 ሆኖ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል ብሏል። የ1954 የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕጉ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየ በመሆኑ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግሥት እና ከወንጀል ፍትሕ ፖሊሲ እንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በዘርፉ ካሉ አዳዲስ አሠራሮችና የቴክኖሎጂ እድገቶች አኳያ ከዘመኑ ጋር በተጣጣመ መልኩ መከለሱ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ባለፉት ዓመታት የአዲስ ሕግ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል። ብዙ ምክክር ተደርጎበት የጸደቀው የሕግ መድብል አዳዲስ አሠራሮችን የሚያስተዋውቅ፤ የወንጀል ምርመራ፣ ክስና ማስረጃ ሥርዓቱን ወደአዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው ሲልም አስገንዝቧል ጽሕፈት ቤቱ።
ባሳለፍነው ሳምንት
Mar 28, 2026 399
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 13 እስከ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • የ ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን እና የሰው ልጅ ታሪክ በጀመረበት ምድር የተገነባውን ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅት ሎጁ የዛሬ 50 እና 60 ዓመት መሠራት የነበረበት ቢሆንም፤ አሁን ስለዘገየን አንቆጭም ማለታቸው ይታወሳል። ይህን ስለሠራንም አንረካም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሩጫችን ገና ብዙ እንደሆነ፣ አፋር ገና እንዳልተነካ አስበን ይህን ጅማሮ ይበልጥ በማላቅ ለማስቀጠል እንተጋለን ሲሉም ተናግረዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከቃና ቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በኢትዮጵያ ከተሞች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነም ገለጻ አድርገዋል። እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸውን ፋይዳም አንስተዋል። • ኢትዮጵያ በማላቦው ጉባዔ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ ወደ ማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ ያቀኑት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ማላቦ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ማኑዌል ኡሳ ኡዙዌን ጨምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጉባዔው ከመጋቢት 18 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ ሲሆን እስከ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቀጥላል። • የልማት ሥራዎች ጉብኝት በባሕር ዳር እና ጎንደር ከተሞች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የባሕር ዳር ከተማን የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያጎሉና ግንባታቸው እየተፋጠኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የመንገድ መሠረተ-ልማት እና የአየር መንገድ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለኢኮኖሚ ዕድገታችን የጎላ ፋይዳ ይኖራቸዋል ሲሉም በወቅቱ ገልጸዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጎንደርን የውኃ ጥም ይቆርጣል፤ የገበሬውን መሬት ያጠጣል፤ የአካባቢውን ምኅዳር ይለውጣል የተባለው የመገጭ የመጠጥ ውኃ ግድብ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተዋል። በዚሁ ወቅት የሀገር ሀብት ፈስሶባቸው መክነው እና ባክነው የቀሩ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ከሞት እያስነሡ ማፋጠን የዚህ መንግሥት ልዩ መለያው ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም የመገጭ ግድብ ምስክር መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም በጎንደር ከተማ አሥተዳደር ሳይና ሳቢያ የገጠር ቀበሌ የተገነቡ የገጠር ኮሪደር ሞዴል ቤቶችን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅትም በአንድ ወር የግንባታ ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀው ይህ ሞዴል መንደር በአካባቢው ለረጅም ዓመታት የቆየውን የጤና ጣቢያ፣ የመብራትና የውኃ አገልግሎት ጥያቄ በተግባር መልሷል ብለዋል። በሀገራችን ከተማው ብቻ ሳይሆን ገጠሩም እኩል እየተዋበ፣ በልማት እየተገነባና በዕድገት ፍኖት ላይ በጽኑ መሠረት እየተራመደ ይገኛልም ነው ያሉት። ይህ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የማሸጋገር ትልቁ ማሳያችን ነው ሲሉም ገልጸዋል። • "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ በአዲስ አበባ 4ኛው "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም፤ የምንፈልገው ድጋፍን ሳይሆን አጋርነትን ነው፤ እርዳታን ሳይሆን ኢንቨስትመንትን ነው! ለባለ ሀብቶች ምቹ፣ ግልጽና ተራማጅ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ አዘጋጅተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ካፒታል፣ ለችሎታ እና ለዕድል በሯን ወለል አድርጋ መክፈቷንም አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ አሁን በፍጥነት ወደ ከፍታ እየገሠገሠች ባለችበት በዚህ ታሪካዊ የዕድገት ጉዞ፤ ለዓለም አቀፍና ለሀገር ውስጥ ባለ ሀብቶች ኢትዮጵያ ለእናንተ ዝግጁ የሆነ፣ በዕድሎችና በስኬቶች የተሞላ ታላቅ የኢንቨስትመንት መሶብ አላት፤ ኑ አብረን እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል! • የትግራይ ክልል አጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) በሰጡት መግለጫም፤ ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ለመጀመርና ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል። በዚህም ከክልሉ ጊዜያዊ አሥተዳደር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀሌ እና በአዲስ አበባ ከ22 ጊዜ በላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ጥረቶች ውስጥ ሂደቱን በክልሉ ለማካሄድ የሚያስችሉ አስቻይ ሁኔታዎች ባለመፈጠራቸው፤ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተወካዮች ምርጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ እንዲከናወን መወሰኑንም አስረድተዋል።
ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት
Mar 26, 2026 187
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በኋላ የታዛቢነት (Observer) ደረጃን አገኝታለች። እ.ኤ.አ በ2006 የውጭ ንግድ ፖሊሲዋን የሚገልጽ ሰነድ ለድርጅቱ አቅርባለች። ሰነዱ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች፣ የወጪና ገቢ ንግድ ሕጎች፣ የቀረጥ፣ ከቀረጥ ውጭ ያሉ የንግድ ገደቦች፣ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ እና የኢንቨስትመንት ሕጎችን ያካተተ ነበር። በኢትዮጵያ እና በዓለም ንግድ ድርጅት መካከል የመጀመሪያው የድርድር ምዕራፍ የተጀመረው እ.አ.አ በ2008 ነው። ከእ.አ.አ 2008 እስከ 2012 በቆየው የቴክኒክ ድርድር ሶስት የስራ ቡድን ስብስባዎች ተካሂደዋል። በዚህ ወቅት የነበረው ድርድር በዋናነት ኢትዮጵያ ስለ ንግድ ሥርዓቷ ማብራሪያ የምትሰጥባቸው እንጂ፣ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘት አልቻሉም። ከእ.አ.አ 2012 እስከ 2019 የሁለቱ ወገኖች ድርድር ተቋርጦ ነበር፤ ለሰባት ዓመታት እንዲቋረጥ ያደረጉ የተለያዩ ምክንያቶች ይነሳሉ። በወቅቱ ስልጣን የነበረው የኢህአዴግ መንግስት "የገበያ ውድቀት" አለ ብሎ ያምን ነበር። ስለዚህም እንደ ባንክ፣ ቴሌኮም እና ኢነርጂ ያሉ ስትራቴጂካዊ ዘርፎች በመንግስት እጅ መቆየት አለባቸው የሚል አቋም ነበረው። ይህ የመንግስት ጽንሰ ሀሳብ ድርጅቱ የተለያዩ ዘርፎች ለውጭ ክፍት መደረግ አለባቸው ከሚለው አቋም ጋር የሚጣጣም አልነበረም። በዓለም ንግድ ድርጅት የተጠየቁ የንግድ ስርዓትን የማዘመን ስራዎች በሚፈለገው መልኩ አለመሄዳቸውም ለድርድሩ መቆም እንደ ምክንያትነት ይነሳል። የለውጡ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያ የአባልነት ድርድር በድጋሚ ነፍስ ዘርቷል። መንግስት በተለያዩ ዘርፎች የወሰዳቸው ጠንካራ የንግድ እና ኢኮኖሚ እርምጃዎች ድርድሩ በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀጥል አድርጓታል። መንግስት እንደ ቴሌኮም፣ ባንክ እና ሎጅቲክስ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጉ በድርጅቱ እንደ ትልቅ ለውጥ የታየ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያን ሕጎች ከድርጅቱ ህጎች ጋር የማጣጣም ስራም ተከናውኗል። ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለው የንግድ ሕግ ማሻሻያ ተደርጎበት ዘመናዊ የንግድ አይነቶች የተካተቱ ሲሆኑ፤ የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መቋቋም የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ላይ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል። ኢትዮጵያ የሸቀጦች ታሪፍ ቅናሽ ሰነዷን አሻሽላ አቅርባለች። ይህም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች የምትጥለው ቀረጥ በምን ያህል መጠንና በስንት ዓመት ውስጥ እንደሚቀንስ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የገባችውን ቃል በተግባር ያሳየችበት ነው። በአሁኑ ሰዓት በዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ኢትዮጵያ በተናጠል እንደ ቻይና፣ ሩሲያ፣ አሜሪካ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችና ካናዳ ካሉ ሀገራት እና ከአውሮፓ ህብረት ጋር የገበያ ተደራሽነት ድርድር እያደረገች ነው። በተደረጉት የተናጥል ድርድሮች ላይም ለኢትዮጵያ አባልነት ሙሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። ከአዕምሯዊ ንብረት ጋር በተያያዘ የፈጠራ ውጤቶችን፣ የንግድ ምልክቶችን እና የባህል እሴቶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ጠንካራ ሕግና ተቋም መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጓል። የጉምሩክ አሰራር የሸቀጦችን ፍሰት ለማሳለጥ የዲጂታል ጉምሩክ አሰራርን የማስፋፋት ስራ በመንግስት በኩል ተከናውኗል። 14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የሚኒስትሮች ስብስባ ከመጋቢት 17 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በካሜሮን ያውንዴ መካሄድ ጀምሯል። በንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክም በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ያውንዴ ገብቷል። ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከስብስባው ጎን ለጎን የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን ሚኒስትሩ ከዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላ (ዶ/ር) ጋር ያደረጉት ውይይትም በዋናነት የሚጠቀስ ነው። በውይይቱ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለድርጅቱ አባል አገራት ከ1200 በላይ ለሚሆኑ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠቷንና ከ419 በላይ የሕግና የፖሊሲ ይዘቶችን ማሳወቋን ጠቁመዋል። የያውንዴው ስብስባ ለኢትዮጵያ የአባልነት ጉዞ የፖለቲካ ድጋፍን ለማሰባሰብ ያስችላታል። በቅርቡ የድርጅቱ አባል ከሆኑ የአፍሪካ እና ሌሎች ሀገራት ጋር የቴክኒክ እና የተሞክሮ ልውውጥ ለማድረግም ምቹ አጋጣሚ ይፈጥርላታል። የያውንዴው ውይይት ኢትዮጵያ በቴክኒክ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በፖለቲካ ደረጃም ለድርድር ዝግጁ መሆኗን የምታሳይበት ነው። የዓለም የንግድ ድርጅት እ.አ.አ በ1995 የተቋቋመ ሲሆን ዋና መቀመጫው ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ነው።ድርጅቱ 166 አባል ሀገራት አሉት። አባል ሀገራቱ የዓለምን 98 በመቶ የንግድ ልውውጥን እንደሚሸፍኑ መረጃዎች ያመለክታሉ። የዓለም ንግድ ድርጅት በዓለም ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው አቅምና ተጽዕኖ እጅግ ከፍተኛ ነው። ድርጅቱ ራሱ ገንዘብ የሚያበድር ባንክ ባይሆንም፣ የዓለምን የንግድ “የጨዋታ ሕግ" በመቅረጽ ረገድ ያለው ሚና ትልቅ መሆኑን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል መሆኗ የገበያ እድሏ እንዲሰፋ ያደርጋል። የኢትዮጵያ ምርቶች በ160+ አባል አገራት ገበያ ውስጥ ያለ አድሎና በዝቅተኛ ታሪፍ እንዲገቡ ዕድል ይሰጣል። ይህ በተለይም ለግብርና ውጤቶችና ለጨርቃጨርቅ ምርቶች ትልቅ በር ይከፍታል። የኢትዮጵያ አባል መሆን ሀገሪቷ ዓለም አቀፍ የንግድ ሕጎችን እንደምታከብር ማረጋገጫ ስለሚሆን፤ ትልልቅ የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ላይ ያላቸው እምነት እንዲጨምር ያደርጋል። ኢትዮጵያ አባል መሆኗ ከሌሎች አገራት ጋር የንግድ አለመግባባቶች ቢገጥሟት፣ በድርጅቱ የክርክር መፍቻ መድረክ አማካኝነት መብቷን ማስከበር ትችላለች። ኢትዮጵያ የንግድ አቅሟን ለመገንባት የሚያግዙ ልዩ ልዩ ሥልጠናዎችንና የቴክኒክ ድጋፎችን ከድርጅቱ ማግኘት ትችላለች። ኢትዮጵያ በያዘችው ፍጥነት እና ቁርጠኝነት ከቀጠለች እ.አ.አ 2026 የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድሯን የማጠናቀቅ እድሏ ሰፊ ነው። የድርድሩ መጠናቀቅ ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማጽደቅ እና የአገር ውስጥ ህጎችን ከድርጅቱ ሕግ ጋር የማጣጣም ስራዎችን ጨምሮ በቀጣይ ምዕራፍ ለሚከናወኑ ስራዎች በር ይከፍታል። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን ውጥኗ ከ23 ዓመታት በኋላ እውን ሊሆን የተቃረበ ሲሆን ድርድሩም ወደ መደምደሚያው ምዕራፍ ደርሷል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 21, 2026 866
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 6 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ማሳሰቢያ በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ስለዚህ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በኃላፊነት ልንጠቀም ይገባል ሲሉ ያሳሰቡት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ባሳለፍነው ሳምንት … ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል የነዳጅ ብክነትን ለመቀነስ ምን ዓይነት ብልኀት መጠቀም ይመከራል? ፕሬዚዳንት ታዬ ያስጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባሳለፍነው ሳምንት የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑን ገልጸው፤ የሕይወት ምሉዕነት የሚረጋገጠው ካለው ላይ ቆርሶ በመስጠት መሆኑን አስገንዝበዋል። ለተቸገሩ መድረስና ለወገን መቆም ትልቅ የመንፈስ ዕርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ መጠናከር እንዳለበትም አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ የተወያዩት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጉብኝት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በእንዶዴ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ እና በኤ ኤም ጂ (AMG) - እንዶዴ የባቡር መሥመር ፕሮጀክቶች ላይ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። እነዚህ በራስ ዐቅም የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነታችንን ከማሻሻል ባለፈ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ያጸናሉ ሲሉም በዚሁ ወቅት በአጽንዖት ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ጋር በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ መሥተዳድሮች፣ ከከተማ አሥተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ሥርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ሥርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1 ሺህ 452 ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሐሴ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ረመዳን ወር ተጠናቅቆ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት የተከበረው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ለበዓሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች የፌደራል፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። #ባሳለፍነው_ሣምንት #ኢዜአ
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3803
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2573
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8362
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6849
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች
Apr 5, 2026 2375
በዮሐንስ ደርበው ✍️ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ‘በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ’ ከሚለው ብኂል የላቁና ቁጭት የወለዳቸው ኢኒሼቲቮች - የቱሪዝም ፀጋን ከመግለጥ ባለፈ የገቢ መጠንን እንዲሁም የሥራ ዕድልን እያሳደጉ ነው። ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ እንደመሆኗ ብዙ ናት። ይህን ሁሉም ሀገራት ስለማያገኙት ዕድለኛም ናት፤ የእኛም ስለሆነች መታደል ነው። የተለያየ የኑሮ ዘይቤ፣ ባህል እንዲሁም ሁሉንም የዐየር ፀባይ ዐቅፋለች። ደግሞም ልዩ ልዩ የተፈጥሮ አቀማመጥ በልዩነት የተቸራት። አሥረጂ ማቅረብ ቢያሻ በሀገሪቱ ከፍተኛ ከሆነው ስሜን ተራራዎች እስከ ዝቅተኛው ስፍራ ዳሎል ያለውን የተፈጥሮ ፀጋ መጥቀስ ሁነኛ ምሥክር ነው። ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ✍️ የተፈጥሮ ችሮታ ለኢትዮጵያ ከብዙ ሥጦታዎቿ መካከል ብሔራዊ ፓርኮችን ብቻ ብናነሳ… የኢትዮጵያ የዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን በጀት መድቦ በቀጥታ በሥሩ 11 ብሔራዊ ፓርኮችን እና ሁለት የዱር እንስሣት መጠለያዎች ያሥተዳድራል። እነሱም፡- 📌 ስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አብያታ ሻላ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ኦሞ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 አልጣሽ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ገራይሌ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ሃላይደጌ ብሔራዊ ፓርክ፤ 📌 ቃፍታ ሽራሮ ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም 👉 ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ እና 👉 ሲንቂሌ የቆርኬዎች መጠለያዎች ናቸው። ብሔራዊ ፓርኮቹና የዱር እንስሣት መጠለያዎቹ የሀገሬው ሀብት ናቸውና፤ እየተንከባከቡ መጠቀም ይገባል። ✍️ መንግሥት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ከላይ የተገለጹትን ብሔራዊ ፓርኮችና ሌሎችንም፤ ከቤት እንስሣት ንክኪ ነጻ በማድረግ፣ ከልቅ ግጦሽ እንዲሁም ከሕገ-ወጥ ዐደን ለመጠበቅ መንግሥት ብዙ ገንዘብ ያወጣል። የሰው ኃይልና የቁሳቁስ ዐቅርቦትንም ያሟላል። ይህም ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ይመሠክራል። በሌላ በኩል የላሊበላ አብያተክርስቲያናት፣ ሶፍዑመር ዋሻን እና የፋሲል አብያተ መንግሥትን ጨምሮ በየክልሎች የሚገኙ ቅርሶችን በመጠገንም እንዲሁ እየተጋ ነው። ከአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎቹ አንዱ የቱሪዝም ዘርፍ ማድረጉም ትኩረቱን ያሳያል። በዚህ ሂደት በየአካባቢው ፀጋዎችን ዕየለየ በርካታ መዳረሻዎችንና የጎብኝ ማረፊዎችን አልምቷል፤ እያለማም ነው። እነዚህም በኢኮኖሚው ብሎም በሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍ ያለ ሚና እያበረከቱ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት፤ በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ የተሠሩ መዳረሻዎችን ለአብነት ብንጠቅስ፤ ‘በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ’ ከሚለው ብኂል የላቁና ቁጭት የወለዳቸው ኢኒሼቲቮች ናቸው። የቱሪዝም ፀጋን ከመግለጥ ባለፈ የገቢ መጠንን እንዲሁም የሥራ ዕድልን እያሳደጉ ነው። ኢትዮጵያ ዛሬ ነገንም እየሠራች ነውና፤ በቱሪዝሙ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት በተለያየ የኢትዮጵያ ክፍሎች መጭውን ትውልድ ባገናዘበ ሁኔታ እየተሳለጡ ነው። በአፍሪካ መዲና በአንድነት እና የወዳጅነት ፓርኮች ጅማሮውን ያደረገው የዘርፉ ልማት፤ ወደ ወንጪ ኢኮቱሪዝም፣ ጎርጎራ፣ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት፣ የሸበሌ ሪዞርት፣ ሶፍዑመር ዋሻ፣ ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፣ የዝሆኖች ዳና ሎጂ፣ የኒዒን ሌ ፓልም ሎጂ ድረስ ወዘተ… ዘልቋል። እንደቀጠለም ነው። እነዚህም ፀጋን ለይቶ ወደ ሃብት በመቀየር ሂደት በመንግሥት ብርታት የለሙ መዳረሻዎች ናቸው። መንግሥት ነባር መዳረሻዎችን በመጠገንና በማደሥ፤ አዳዲስ መዳረሻ በመገንባት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም አልሠሠተም፤ ብዙ እየሠጠ ነው። ✍️ ከቱሪዝም ዘርፍ አንጻር የሕብረተሰቡ ሚና ቱሪዝም በተፈጥሮው ከበርካታ ጉዳዮች ጋር ይተሣሠራል። በእጅጉ ሰላም ይሻል፤ የሰላም ባለቤት ደግሞ ሕዝቡ ነው። ዘርፉ የቅርሶችንና መዳረሻዎችን ልማትና እንክብካቤም ይሻል። ለዘርፉ የሚሰጥ ትኩረት ሀገርንም፤ ሕዝብንም ይጠቅማል፤ ጥቅሙ ከዕለት ጉርስ እስከ ጥሪት ይዘልቃል። በዚህ ሂደት ሕዝቡ በየአካባቢው ያሉ ብሔራዊ ፓርኮችን፣ ቅርሶችን እና የቱሪስት መዳረሻዎችን የኔ ብሎ መጠበቅ ይኖርበታል። ለምሳሌ፡- ብሔራዊ ፓርክ ወይም በመዳረሻ ላይ ጉዳት ቢደርስ በቀጥታ ተጎጂው የአካባቢው ነዋሪ ነው። ምክንያቱም ቱሪስት ካልሄደና ገቢ ካልተገኘ ገቢ ይደርቃልና።
የጀጎል አለም አቀፍ ቅርስን የታደገው ሀገራዊ ለውጥ
Apr 4, 2026 228
የስልጣኔ መነሻ የጥበብ መፍለቂያ የሆነችው የምስራቋ ፈርጥ ሀረር የንግድ፣ የፖለቲካና ማህበራዊ ትስስር ማዕከል ሆና በትውልድ ቅብብሎሽ ከአንድ ሺህ አመታት በላይ የተሻገረች እድሜ ጠገብ ከተማ ነች። በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በምስራቅ አፍሪካ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርትና የንግድ ማዕከል የነበረችው ከተማዋ በርካታ ቋሚና ተንቀሳቃሽ እንዲሁም የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቁሳዊና ሀይማኖታዊ ቅርሶችን የያዘች ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ ነች። ከእነዚህ ቅርሶች መካከል ጥንታዊ የስነ-ህንፃ የጥበብ፣ የከተማ ፕላን፣ ባህላዊ የመሬት አጠቃቀም፤ አካባቢያዊ መስተጋብርና የስልጠኔ መገለጫ በሚል እኤአ በ2006 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም ዩኔስኮ በአለም አቀፍ ቅርስነት የተመዘገበው የጀጎል ቅርስ ይጠቀሳል፡፡ ቅርሱ ምንም እንኳን በኪነ ህንፃ ጥበብ በላቁ በአርቆ አሳቢ አባቶች እንዳይፈርስና ሚዛኑን ጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ በተመረጠ ድንጋይ እና አፈር በልዩ ጥበብ የተገነባ ቢሆንም በጥበቃና እንክብካቤ ጉድለት ምክንያት ከግማሽ ምዕተ አመታት በላይ እድሜን ባስቆጠረው ቅርስ ላይ አደጋ ተጋርጦበት ቆይቷል። በቅርሱ ውስጣዊ እና ውጫዊ ክፍሎች የህገ-ወጥ ግንባታዎች መበራከትና በሌሎች ምክንያቶች በደረሰበት ጉዳት የጥንት ስልጣኔ ምልክት የሆነው አለም አቀፉ የጀጎል ቅርስ ከዩኔስኮ የአለም ቅርስነት እስከመሰረዝ የደረሰ አደጋ ተደቅኖበት ነበር። ሆኖም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በአዲስ እሳቤ፤ በተደመረ አቅምና በላቀ ቁርጠኝነት፤ ህዝብን በማሳተፍ ከመንግስት ምንም አይነት በጀት ሳይመደብለት ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ማልማት ተቻለ። አሁን ላይ እነኛ በሸራና በጨርቅ በተሰሩ ህገወጥ ግንባታዎች ተወሮ የነበረው 3ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የጀጎል ግንብ ዙሪያ በአበቦችና ቅርሱን በሚያስውቡ ስራዎች ደምቀዋል። በዚህም አባቶች ከዘመኑ ቀድመው ዛሬም ድረስ ግርምትን በሚያጭር ጥበብ አንፀው ያኖሩት ይህንን የሀገር ሀብት በመታደግ ትውልዱን ከታሪክ ተወቃሽነት ወደ ዳግም ታሪክ ሰሪነት እንዲሸጋገር ማድረግ ተችሏል። ስራውም የትላንትን መሰረት ሳያናጋ፤ የቀድሞ አባቶችን ጥበብና ስልጣኔ ሳይጋፋና ሳይዘነጋ ጥንታዊውን ከዘመናዊ ጋር አዋህዶ ቅርስ መገኛ ለሆኑ ሌሎች አካባቢዎችም ተምሳሌት በሚሆን ደረጃ አስደናቂ ስራ ተከናወነ። የአካባቢውን ሀብትና እውቀት በመጠቀም እውን የተደረገው ይህ ስራ በእያንዳንዱ የሀረሪ ጥንታዊ ቤቶች በሚገኙ የታሪክ አሻራዎችና የባህል መገለጫዎች እንዲደምቅም ሆኗል። ይህ ትውልድ ተሻጋሪ ስራ ቅርሱን ከአደጋ ከመታደግ ባለፈ ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከግለሰብ እስከ ማህበራትና የዳያስፖራ አባላት ድረስ ሁሉም በያገባኛል ስሜት አሻራውን ያኖረበት ዘመን ተሻጋሪ ፕሮጀክት ነው። ይህም በቅርሱ ላይ የእኔነት ስሜት እንዲጎለብት በማድረግ የእይታ ለውጥ እንዲመጣ ያስቻለና ቀደም ሲል የነበሩ የግለኝነት አስተሳሰቦችን በመቅረፍ የወል እሳቤ እውን የሆነበት ፕሮጀክት ሆኖ ታይቷል። ዛሬ ላይ እነኛ የቆሻሻ መጣያ የነበሩ እና በአካባቢው ለማለፍ ከባድ የነበሩ የጀጎል መንገዶች ፀድተው ውብ ሆነዋል። ይዘታቸውን ለቀው የነበሩ ቅርሶችም የአለም ቅርስነት ክብርና መስፈርትን በሚመጥን ደረጃ ታድሰዋል። ዛሬ የጀጎል ነዋሪ እንደቀድሞ አካባቢውን ለቆ ለመሄድ ሳይሆን መኖርን የሚመርጥባት የወጣውም መመለስን የሚመኝባት ምቹ አካባቢ ሆናለች። የመቻል ምልክት የትብብር ውጤትና የአብሮነት ጉልበት በተግባር የታየበት የጁገል መልሶ ልማት ጥንታውን መንደር ለነዋሪዎች ምቹ ለጎብኚዎች ተመራጭ የጉብኝት ስፍራ እንዲሆን ማድረግ ተችሏል። በለውጡ መንግስት በአዲስ መልክና ቀለም የተዋበው ጀጎል የሀረርን ቀደምት ስልጣኔ እየመሰከረ የሀገርንም ገፅታ እየገነባ ይገኛል።