ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
መንግሥት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ ነው
Mar 8, 2026 6
ጅግጅጋ፣ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል የሴቶች እና ህጻናት ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኡበህ አብዱረህማን ተናገሩ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8) "50ኛ ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ተከበረ። የሶማሌ ክልል የሴቶች እና ህጻናት ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኡበህ አብዱረህማን እንደገለጹት፣ መንግሥት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ ነው። የሴቶችን ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሠሩ ሥራዎች አበረታች ለውጦች መገኘታቸውንም ነው የተናገሩት። በሶማሌ ክልል ሴቶችን ለአመራርነትና ውሳኔ ሰጪነት በማብቃት በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ የላቀ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል። ባለፉት አመታት የተገኙትን የሴቶች ተሳትፎ የሚያጠናክሩ ስኬቶች ማስቀጠልና ማጎልበት እንደሚገባም ተናግረዋል። ያለ ሴቶች ንቁ ተሳትፎ ኢትዮጵያ ያቀደችውን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ የማይታሰብ መሆኑን አንስተው በዚህ ረገድ ጠንካራ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል ዘሀራ ዩሱፍ ሴቶች የቤተሰብና የህብረተሰብ ምሰሶ እንደሆኑ ተናግረው እናቶች አምራች ትውልድ በማፍራት የሀገር ባለውለታ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሴቶች መንግሥት እያከናወነ ያለውን ልማት በመደገፍ የድርሻቸውን እንዲወጡ ለይላ ሂስ አህመድ ጠየቀዋል፡፡
የሥርዓተ ጾታ እኩልነትንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)
Mar 8, 2026 26
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የሥርዓተ ጾታ እኩልነትንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ወደ ሀገር ውስጥና ውጭ ሀገራት በሴቶች ብቻ የሚመሩ ስምንት በረራዎች እንደሚከናወን አስታውቋል፡፡ ሚኒስትሯ ይህንን የገለጹት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (ማርች ምክንያት በማድረግ በሴቶች ብቻ ለሚመራው የበረራ ቡድን በስካይላይት ሆቴል በተዘጋጀው የሽኝት መርሃ ግብር ላይ ነው። አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት በሴቶች የሚመሩ ስምንት በረራዎችን ያደርጋል። በዚህ ወቅት የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ አየር መንገዱ የኢትዮጵያ ኩራት በመሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሀገርን ስም ከማስጠራት ባለፈ፣ ሴቶችን በማብቃት ረገድ አርዓያነት ያለው ተግባር እያከናወነ ይገኛል። አየር መንገዱ የጾታ እኩልነትን፣ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሴቶችን ለማብቃትና እኩል ዕድል ለመፍጠር የግሉ ዘርፍም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል። መንግስት ሴቶች ሙሉ አቅማቸውን እንዲያወጡ የሚያስችል ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ መሆኑን ጠቁመው፤ የስርዓተ ፆታ እኩልነትና የሴቶችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሴቶች ተቋም የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ጃኔት ኪም በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሴቶች ብቻ የተመራ በረራ ማድረጉ ሴቶች ዕድሉ ከተሰጣቸው የማይወጡት አቅም እንደሌለ ማሳያ ነው ብለዋል። አየር መንገዱ በአቪዬሽን ዘርፍ እያከናወነ ካለው የላቀ ተግባር በተጨማሪ ሴቶችን በዘርፉ ለማብቃት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የእኩልነት መርህን በተግባር ለዓለም ያሳየ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፤ የበረራ መርሃ ግብሩ ከፓይለት እስከ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪነት ያለውን ሂደት ጨምሮ ሙሉ በሙሉ በሴቶች የሚመራ መሆኑን ገልጸዋል። አየር መንገዱ ላለፉት ተከታታይ ዓመታት በተመረጡ ሀገራት በሴቶች ብቻ የተመራ በረራ ሲያካሂድ መቆየቱን አስታውሰው፤ ዘንድሮም ወደ ሀገር ውስጥና ውጭ ሀገራት ስምንት በረራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአየር መንገዱ 40 በመቶ ሰራተኞች እንዲሁም 35 በመቶ አመራሮች ሴቶች ሲሆኑ የሴት ፓይለቶች ቁጥርም 95 ደርሷል። ይህ የበረራ መርሃ ግብር ሴቶች በአቪዬሽን ዘርፉ ያላቸውን ተሳትፎ ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም ተመላክቷል።
በቀጣናው የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው -ኢጋድ
Mar 8, 2026 23
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂን ጨምሮ በቀጣናው የሴቶችን የአመራርና ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው። "መብቶች፣ ፍትህ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሴቶችን ቀን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፏል። ኢጋድ ለሴቶች አመራር ሰጪነት፣ አይበገሬነት እና በቀጣናው ሰላም፣ ብልጽግና እና ለውጥ ለማምጣት እያበረከቱት ላለው አስተዋጽኦ ክብር እና እውቅና እንደሚሰጥ ገልጿል። በኢጋድ ሴቶች በቀጣናው አመራር ሰጪነት ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። የኢጋድ የሰላም፣ ግብርና፣ ዲጂታል ደህንነት፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና መሬት አስተዳደር ፎረሞች እንዲሁም የኢጋድ የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂ ጨምሮ የተለያዩ ኢንሼቲቮች እየተገበረ መሆኑን አመልክቷል። የሴቶች ድምጽ እንዲሰማ እና መሉ ተሳትፏቸው እንዲረጋገጥ የሚያግዙ መድረኮችን መፍጠሩን ነው የኢጋድ ሴክሬተሪያት በመረጃው ያስታወቀው።
የትግራይ ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል -ምሁራን
Mar 8, 2026 58
ቦንጋ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ክልል ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ በሀገር ደረጃ እየተመዘገበ ካለው ሁሉን አቀፍ ልማትና ሰላም ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባው መግለፃቸው ይታወቃል። ለክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ልማትና ተጠቃሚነት መንግስት ቁርጠኛ አቋም ይዞ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህወሃት ቡድን ለሌላ ጦርነት እየሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያ በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግኑኝነት ትምህርት ክፍል መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ያሬድ አያሌው (ዶ/ር)፣ የተራማጅነት እሳቤ የሌለው የህወሃት ቡድን ዘመኑን ለሚመጥን የፖለቲካ እሳቤ ዝግጁነት የሌለው መሆኑን ባለፉት ዓመታት ማየት ተችሏል ብለዋል። ይህም በመሆኑ በተለይም የትግራይ ክልልና ህዝቡ የለውጡ ተጠቃሚ እንዳይሆን መሰናክል ሆኗል ሲሉ ጠቅሰዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን ያለውን የጸና አቋም የገለጹበት መሆኑን አንስተው፣ የህወሃት ቡድን ከዚህ በተቃራኒ ቆሞ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም የህወሃትን ቡድን ያረጀ አስተሳሰብ ለመቀየር በተለይም የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ተነሳሽነት ወስዶ መንቀሳቀስ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። የህወሃት ቡድን የትግራይን ሕዝብ በተለይም ወጣቱን ሀይል እንደማሲያዣ በመጠቀም አሁን እንደሀገር እየተመዘገበ ካለው የልማት፣ የሰላምና የአንድነት ጉዞ ተነጥሎ እንዲኖር እያደረገው መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የጥፋት ቡድኑን በቃ ሊለው ይገባል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ ወደ ሰላሙ እንዲመለስ እና የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጽኑ ፍላጎት እንዳለው ያሳያል ያሉት ዶክተር ያሬድ ፤ ህዝቡም የመንግስትን ጥረት ደግፎ ለለውጥ መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ የህወሃትን ቡድን እኩይ ዓላማ ማክሸፍ የሚችለው ጠንካራ ትብብርና ፅኑ ትግል ማድረግ እንዳለበት ጠቁመው፤ ይህንን ለማድረግ ጊዜ ማባከን አይገባም ብለዋል። በዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ አዲሱ ፍሪንጆ (ዶ/ር) ፤ እንዳሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክልሉ ተፈጥሮ የነበረውን የሰላም እጦት ምክንያት ለይተው ለዘላቂ ሰላም ጠቃሚ ናቸው ያሏቸውን ሃሳቦች ማንሳታቸው ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። የትኛውም የፖለቲካ አስተሳስብ ከዘመኑ ጋር ተራማጅ መሆኑን ያነሱት ምሁሩ፣ የህወሃት ቡድን ተቀባይነት በሌለውና በቆየ አስተሳሰብ ዛሬም እቀጥላለሁ ማለቱ የማይለወጥና ቆሞ ቀርነቱን ያሳያል ብለዋል። ባረጀ አስተሳሰቡ ቀደም ሲል በፈጠረው ግጭት የትግራይ ክልል ህዝብ ከልማት እንዳይጠቀም ማደረጉን አስታውሰው፣ ሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ በተለይ ወጣቱ ቡድኑን ሌላ ግጭት አንፈልግም ሊለው ይገባል ብለዋል። ወጣቶች ሁሌም ለሰላም ሊቆሙ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክትና ማብራሪያ ከትግራይ ክልል ነባራዊ ሁኔታ ባሻገር የኢትዮጵያን የፖለቲካ አካሄድና ሥርዓት ያሳየ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በርሁን ናቸው። ይህም ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸው፤ በተለይ የትግራይ ወጣቶች በአረጀ አስተሳሰብ ከተቸነከረው የህወሃት ቡድን ራሱን በማላቀቅ ለክልሉ ሰላምና የተሻለ አማራጭ መቆም እንዳለበት ገልጸዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች እያካሄዱት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት ያግዛል - ምሁራን
Mar 8, 2026 78
አሶሳ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች እያካሄዱት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እንደሚያግዝ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናገሩ። 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማከናወን የዕጩዎች ምዝገባ የተጠናቀቀ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ደግሞ የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ ይገኛል። በምርጫው ዜጎች የተሻለ ሃሳብ እና ፖሊሲ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ እንዲያስችላቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮችን እያከናወኑ መሆናቸው ይታወቃል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን እንደተናገሩት፤ ምርጫን በህገ መንግስቱ መሠረት በተያዘለት ገደብ ማከናወን አንዱ የዴሞክራሲ መገለጫ ነው። በዩኒቨርሲቲው የፌዴራሊዝም መምህር ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉት የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮች ህብረተሰቡ ስለሚመርጠው ፓርቲ የተሻለ ግንዛቤ እንዲይዝ ያደርጋሉ ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን በነፃነት እያከናወኑት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት የሚያግዝ እና የፓርቲዎች ማኒፌስቶ ለመራጮች ተደራሽ እንዲሆን ያግዛል ነው ያሉት። የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅሰቀሳ ወቅት የሚያነሱት የምረጡኝ ቅስቀሳ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት ያለው መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነምግባርን በማክበር በሃሳብ ብቻ መከራከርን መልመድ አለባቸው ያሉት ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ፤ ሀገርን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ጠቅሰዋል። ሌላው በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህር አበበ አኖ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ምርጫ ለአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች መፍትሔ ያመጣል ተብሎ ስለሚጠበቅ የዜጎችን ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው ብለዋል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዜጎች አሳሳች የሆነ አስተሳሰብ እንዳይዙ በማድረግ ግልፅ ፖሊሲና በምርጫው ቢያሸንፉ ሊፈጽሙት በሚገባው ትክክለኛ ፖሊሲ ላይ ትኩረት አድርገው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመዋል።
ፖለቲካ
የትግራይ ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል -ምሁራን
Mar 8, 2026 58
ቦንጋ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ክልል ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ በሀገር ደረጃ እየተመዘገበ ካለው ሁሉን አቀፍ ልማትና ሰላም ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባው መግለፃቸው ይታወቃል። ለክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ልማትና ተጠቃሚነት መንግስት ቁርጠኛ አቋም ይዞ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህወሃት ቡድን ለሌላ ጦርነት እየሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያ በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግኑኝነት ትምህርት ክፍል መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ያሬድ አያሌው (ዶ/ር)፣ የተራማጅነት እሳቤ የሌለው የህወሃት ቡድን ዘመኑን ለሚመጥን የፖለቲካ እሳቤ ዝግጁነት የሌለው መሆኑን ባለፉት ዓመታት ማየት ተችሏል ብለዋል። ይህም በመሆኑ በተለይም የትግራይ ክልልና ህዝቡ የለውጡ ተጠቃሚ እንዳይሆን መሰናክል ሆኗል ሲሉ ጠቅሰዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን ያለውን የጸና አቋም የገለጹበት መሆኑን አንስተው፣ የህወሃት ቡድን ከዚህ በተቃራኒ ቆሞ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም የህወሃትን ቡድን ያረጀ አስተሳሰብ ለመቀየር በተለይም የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ተነሳሽነት ወስዶ መንቀሳቀስ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። የህወሃት ቡድን የትግራይን ሕዝብ በተለይም ወጣቱን ሀይል እንደማሲያዣ በመጠቀም አሁን እንደሀገር እየተመዘገበ ካለው የልማት፣ የሰላምና የአንድነት ጉዞ ተነጥሎ እንዲኖር እያደረገው መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የጥፋት ቡድኑን በቃ ሊለው ይገባል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ ወደ ሰላሙ እንዲመለስ እና የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጽኑ ፍላጎት እንዳለው ያሳያል ያሉት ዶክተር ያሬድ ፤ ህዝቡም የመንግስትን ጥረት ደግፎ ለለውጥ መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ የህወሃትን ቡድን እኩይ ዓላማ ማክሸፍ የሚችለው ጠንካራ ትብብርና ፅኑ ትግል ማድረግ እንዳለበት ጠቁመው፤ ይህንን ለማድረግ ጊዜ ማባከን አይገባም ብለዋል። በዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ አዲሱ ፍሪንጆ (ዶ/ር) ፤ እንዳሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክልሉ ተፈጥሮ የነበረውን የሰላም እጦት ምክንያት ለይተው ለዘላቂ ሰላም ጠቃሚ ናቸው ያሏቸውን ሃሳቦች ማንሳታቸው ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። የትኛውም የፖለቲካ አስተሳስብ ከዘመኑ ጋር ተራማጅ መሆኑን ያነሱት ምሁሩ፣ የህወሃት ቡድን ተቀባይነት በሌለውና በቆየ አስተሳሰብ ዛሬም እቀጥላለሁ ማለቱ የማይለወጥና ቆሞ ቀርነቱን ያሳያል ብለዋል። ባረጀ አስተሳሰቡ ቀደም ሲል በፈጠረው ግጭት የትግራይ ክልል ህዝብ ከልማት እንዳይጠቀም ማደረጉን አስታውሰው፣ ሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ በተለይ ወጣቱ ቡድኑን ሌላ ግጭት አንፈልግም ሊለው ይገባል ብለዋል። ወጣቶች ሁሌም ለሰላም ሊቆሙ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክትና ማብራሪያ ከትግራይ ክልል ነባራዊ ሁኔታ ባሻገር የኢትዮጵያን የፖለቲካ አካሄድና ሥርዓት ያሳየ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በርሁን ናቸው። ይህም ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸው፤ በተለይ የትግራይ ወጣቶች በአረጀ አስተሳሰብ ከተቸነከረው የህወሃት ቡድን ራሱን በማላቀቅ ለክልሉ ሰላምና የተሻለ አማራጭ መቆም እንዳለበት ገልጸዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች እያካሄዱት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት ያግዛል - ምሁራን
Mar 8, 2026 78
አሶሳ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች እያካሄዱት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እንደሚያግዝ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናገሩ። 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማከናወን የዕጩዎች ምዝገባ የተጠናቀቀ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ደግሞ የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ ይገኛል። በምርጫው ዜጎች የተሻለ ሃሳብ እና ፖሊሲ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ እንዲያስችላቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮችን እያከናወኑ መሆናቸው ይታወቃል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን እንደተናገሩት፤ ምርጫን በህገ መንግስቱ መሠረት በተያዘለት ገደብ ማከናወን አንዱ የዴሞክራሲ መገለጫ ነው። በዩኒቨርሲቲው የፌዴራሊዝም መምህር ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉት የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮች ህብረተሰቡ ስለሚመርጠው ፓርቲ የተሻለ ግንዛቤ እንዲይዝ ያደርጋሉ ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን በነፃነት እያከናወኑት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት የሚያግዝ እና የፓርቲዎች ማኒፌስቶ ለመራጮች ተደራሽ እንዲሆን ያግዛል ነው ያሉት። የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅሰቀሳ ወቅት የሚያነሱት የምረጡኝ ቅስቀሳ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት ያለው መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነምግባርን በማክበር በሃሳብ ብቻ መከራከርን መልመድ አለባቸው ያሉት ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ፤ ሀገርን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ጠቅሰዋል። ሌላው በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህር አበበ አኖ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ምርጫ ለአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች መፍትሔ ያመጣል ተብሎ ስለሚጠበቅ የዜጎችን ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው ብለዋል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዜጎች አሳሳች የሆነ አስተሳሰብ እንዳይዙ በማድረግ ግልፅ ፖሊሲና በምርጫው ቢያሸንፉ ሊፈጽሙት በሚገባው ትክክለኛ ፖሊሲ ላይ ትኩረት አድርገው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመዋል።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል - የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 92
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ይጠቅመናል ያልነውን ለመምረጥ የምርጫ ካርዳችንን መውሰዳቸውን በአዲስ አበባ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያካሄድ አስታውቋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎች ማስመዝገባቸውንም መግለጹ ይታወሳል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ተጀምሯል። የኢዜአ ሪፖርተሮች በከተማዋ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች በመዘዋወር የመራጮች የምዝገባ ሂደት ቅኝት አድርገዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ዮሀንስ አሰፋ እንደተናገረው፤ ምርጫ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ የእድገትና የልማት ጉዞ የሚያሸጋግር ፓርቲ የምንመርጥበት ኹነት ነው። ስለሆነም ኢትዮጵያን በልማት ሊያሳድግና ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያደርስ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ብሏል። ዕድሜው ለመራጭነት የደረሰ ሁሉ ምርጫ ካርድ በመውሰድ በንቃት መሳተፍ እንዳለበት አመልክቷል። በጠቅላላ ምርጫ ለሀገር ይበጃል የምለውን ለመምረጥ የምርጫ ካርዱን መውሰዱን የተናገረው ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ ኤልዔዘር ደጉ ነው። ወጣቶች ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም መምረጥ እንዲችሉ ምርጫ ካርዳ እንዲወስዱም ጥሪ አቅርቧል። በጉለሌ ክፍለ ከተማ የመራጭነት ካርድ የወሰዱት አቶ ወርቁ ይርጋው በበከላቸው፤ ኢትዮጵያን ለወደፊት የሚመራና ወደ ተሻለ የዕድገት ደረጃ ሊያሻግር የሚችል ፓርቲ ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ ምርጫ ለሰላምና ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስፈላጊ በመሆኑ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የተናገሩት ደግሞ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ነዋሪዋ ወይዘሮ አማረች በሱፍቃድ ናቸው፡፡ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ነዋሪ ወጣት እንደሻው ነጋሽ በበኩሉ፤ በመጪው ጊዜ ለዕድገት የሚሰራ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ በመወሰዴ ደስተኛ ነኝ ብለዋል፡፡ የዘንድሮ ምርጫ በዲጂታል የታገዘ መሆኑ ታአማኒነትን የሚጨምርና የተለያዩ መረጃ መጣረሶችን የሚያስቀር መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Mar 7, 2026 94
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተባባሪነት የተዘጋጀው ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' የተሰኘ መጽሐፍ ምረቃ መርሃ ግብር በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል። በመጽሐፉ ምረቃ መርሃ ግብር ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት፤ መጽሀፉ በሀሳብም ሆነ በይዘት የተሳካለት የታሪክ ካስማ ነው ብለዋል። በ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ላይ ታሪክ ሊይዛቸው የሚገቡ ቁምነገሮች መካተታቸውን ገልጸዋል። መጽሐፉ ታሪክ የዘነጋቸውን የዓድዋ ጀግኖች በቅጡ በመዘከር ለማስታወስ ያደረገው ጥረትም የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። የመጽሐፉ ጽንሰ ሃሳባዊ ቁምነገሮችም የኢትዮጵያዊነትን መንፈስ የሚያሰርጽ ለአዲስ ተስፋና ምኞት የሚያነሳሳ የታሪክ ሰነድ መሆኑን አንስተዋል። ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ዛሬን የምንሰራበትና ነገን የምንከተልበት ኃያል መነጽር መሆኑን አስረድተዋል። የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ መጽሐፉም የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ፋይዳ አመላክቷል ብለዋል። መጽሐፉም የዕውቀት ማስፋፊያ፣ የጎደለ መሙያ፣ ራስን መፈተሻ፣ ራስን ለመመርመር የሚያነሳሳና ምክንያታዊ እሳቤን የሚያጎለብት ሰነድ መሆኑንም ጠቁመዋል።
''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ስሁት የታሪክ አረዳድን ለማረም ትልቅ ፋይዳ አለው
Mar 7, 2026 90
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ለሕትመት መብቃቱ ስሁት የታሪክ አረዳድን ለማረም ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተባባሪነት የተዘጋጀው ''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' የተሰኘ መጽሐፍ ተመርቋል። በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተዘጋጀው የመጽሐፉ ምረቃ መርሃ ግብር ላይ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። በመጽሐፍ ላይ ምርቃት ላይ ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፣ ሀጎስ አብርሀ (ዶ/ር)፣ ደቻሳ አበበ (ዶ/ር) እና የመጽሐፉ ደራሲ አሻግሬ ገብረወልድ (ዶ/ር) ምልከታቸውን አጋርተዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፤ የዓድዋ ድል ታሪክ ቀያሪ ወታደራዊ ድል ብቻ ሳይሆን ቅኝ ግዛትን የሰበረ የነፃነት ፈር ቀዳጅ የእኩልነት ዓርማ ነው ብለዋል። ''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ለሕትመት መብቃቱም ስሁት የታሪክ አረዳድን ለማረም ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። በመጽሐፉም ቅድመ አያቶችን በዓድዋ ተራሮች የተቀዳጁትን አንጸባራቂ ድልና በርካታ ጉዳዮችን ቀለል ባለ አቀራረብ ተቀንብቦ ለተደራስያን መቅረቡን ተናግረዋል። የዓድዋ ድል ለሀገረ መንግስትና የወል ትርክት ግንባታ ወሳኝ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በመጽሐፉም የታሪክ ጉድለቶችን በመሙላት የዓድዋ ድልን ምሉዕነት በሚያሳይ መልኩ ተተርኮ ቀርቧል ብለዋል። ሌላኛው በመጽሐፉ ላይ ዳሰሳ ያቀረቡት የታሪክ ምሁር ሀጎስ አብርሀ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በመጽሐፉ የዓድዋ ድልን ከማወዳደር ይልቅ የጋራ ታሪክና የሁሉም ኢትዮጵያዊያን መሆኑን በተግባር አትቷ ብለዋል። በመጽሐፉ ላይ ተቀንብበው የቀረቡ ሃሳቦችም ለቀጣይ ጥናትና ምርምር እንዲሁም አሰባሳቢ ትርክት ግንባታን ለማጎልበት በማጣቀሻነት የሚያገለግል መሆኑን ገልጸዋል። የታሪክ ምሁር ደቻሳ አበበ (ዶ/ር)፤ በመጽሐፉ ላይ የተከተቡ ወሳኝ ጽንሰ ሃሳቦች የዓድዋ ድልን በአግባቡ በመተረክ የትውልዱን የታሪክ አረዳድ የሚቀርጽ ነው ብለዋል። ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ መጽሐፍ ደራሲ አሻግሬ ገብረወልድ (ዶ/ር)፤ የመጽሐፉ መታሰቢያነት ለኢትዮጵያ ሉዓላዊ አንድነት መስዋዕትነት ለከፈሉ ሆናል ብለዋል። በጽሐፉም የተለያዩ ሰነዶችን በማጣቀስ የዓድዋን የድል ታሪክ በቅጡ የከተበና ለአዳዲስ የታሪክ ትናትና ምርምር ሥራዎች መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ለስኬት እንዲበቃ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
በምርጫ ካርዳችን የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት ተዘጋጅተናል- ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 115
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦በምርጫ ካርዳችን የሚበጀንን በመምረጥ የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት ተዘጋጅተናል ሲሉ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ለስኬታማነቱ በቅንጅት እየተሠራ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ዛሬ የመራጮች ምዝገባ መጀመሩ ይታወቃል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች ፤ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ተሳትፈን ዲሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀምና የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት የመራጭነት ካርድ ወስደናል ብለዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ዘሪሁን ሎሪሶ፤ በምርጫው ሂደት የአንድ ሰው ድምጽ ትልቅ ድርሻ እንዳለው በመረዳት በመራጭነት መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ምርጫው በቀጣይ ሀገሪቱን የሚመራ ፓርቲን ወደ ስልጣን ለማምጣት ብቸኛ መንገድ በመሆኑ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀምና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት መወሰናቸውን ነው የተናገሩት። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ በመገናኛ ብዙሃን እያካሔዱ ባለው የክርክር መድረክ ፕሮግራማቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁን በመሆኑ የሚበጀንን ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስደናል ነው ያሉት። ወይዘሮ የኔዓለም ሳሙኤል በበኩላቸው፤ የምፈልገውን ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት የመራጭነት ካርድ መውሰድ የግድ በመሆኑ ወደ ምርጫ ጣቢያው በመምጣት ተመዝግቤ ካርድ ወስጃለሁ ብለዋል። ምርጫው ፍትሐዊ፣ ሰላማዊና ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻችንን ለመወጣትና ለሚበጀን የፖለቲካ ፓርቲ ድምፃችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል ሲሉም ተናግረዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አማኑኤል ፊሊጶስ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት በመገናኛ ብዙሃን የሚደረጉ ክርክሮች የተሻለ አማራጭ ያለው የፖለቲካ ፓርቲን ለመለየት የሚያስችል ነው ብለዋል። በመሆኑም የነገዋን ኢትዮጵያ መፃኢ ዕድል በምርጫ ካርዳቸው ለመወሰን በጉጉት እየተጠባበቁ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ለስኬታማነቱ በቅንጅት እየተሠራ ነው
Mar 7, 2026 76
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ለስኬታማነቱ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ። ይህ የተባለው "የዴሞክራሲ ባህልን በምርጫ መገንባት" በሚል ርዕስ በተዘጋጀ የፓናል ውይይት ላይ ነው። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል የፓናል ውይይቱ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ያለው 5ኛው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት አካል ሲሆን፥ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ እንደገለጹት፥ ምርጫ የአንድ ወቅት ተግባር ቢሆንም ሂደቱና ከምርጫው በኋላ የሚከናወኑ ተግባራት ለሀገር ግንባታ ወሳኝ ናቸው። የምርጫ ሂደቱ የሕግ የበላይነት የተረጋገጠበት፣ መቻቻልና መግባባት የሰፈነበት እንዲሆን የተጀመሩ ቅንጅታዊ አሠራሮች መጠናከር እንዳለባቸው አስረድተዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚኖረውን አዎንታዊ ሚና ማጉላት እንደሚገባ ጠቅሰው፥ ለዚህም በተቋማት መካከል የተናበበ ሥራ ወሳኝ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ንዋይ በበኩላቸው፥ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ ሰፋፊ የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። የምርጫ መርኃ ግብሩ በጊዜ ሰሌዳው መሠረት እንዲፈጸም ቦርዱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል። እስካሁን ባለው ሂደት የእጩዎች ምዝገባ ተደራሽነትን ባረጋገጠ መልኩ መጠናቀቁንና ለመራጮች ምዝገባም የተለያዩ አማራጮች መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። በተጨማሪም የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሀሳቦቻቸውን በመገናኛ ብዙኃን የሚያስተዋውቁበት ምቹ የሥራ ምኅዳር መፈጠሩን በማንሳት፥ ይህም የዴሞክራሲ ባህል እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ እንዳሉት፤ በምርጫው ሂደት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የነቃ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በትኩረት እየተሠራ ነው። ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ድርጅቶቹ ያላቸውን ሚና እንዲያጎለብቱ የተለያዩ ሥርዓቶች መዘርጋታቸውን በመግለፅ፥ ባለሥልጣኑ ለዚህ የሚረዳ ራሱን የቻለ ዕቅድ አውጥቶ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አስረድተዋል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አሕመድ ሁሴን በበኩላቸው፥ ሕዝቡ በምርጫው ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ለማስገንዘብ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። ምርጫ ዜጎች ተወካዮቻቸውንና መሪዎቻቸውን በድምፃቸው በመምረጥ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን እውን መሆን የሚያረጋግጥና ለሀገር ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አበራ ኃይለማርያም፥ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታዛቢዎችን ቁጥር በላቀ ሁኔታ ከፍ ለማድረግ ጥረት መደረጉን ገልጸዋል። በተለይም የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውንና ሂደቱ ፍትሐዊና ተአማኒ እንዲሆን የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት ላይ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።
ሁሉም ዜጋ በምርጫው የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ሀገራዊ ግዴታውን መወጣት ይኖርበታል-የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 159
ሚዛን አማን፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፡- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ዜጋ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ሀገራዊ ግዴታውን መወጣት ይኖርበታል ሲሉ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መራጮች የምርጫ ካርድ መውሰድ ጀምረዋል በግንቦት ወር ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ መጀመሩ ይታወቃል። ኢዜአ በሚዛን አማን ከተማ በተደራጁ የምርጫ ጣቢያዎች በመዘዋወር ካርድ ለመውሰድ ወደ ጣቢያዎቹ ያቀኑ መራጮችን አነጋግሯል። ተመዝግበው ካርድ ለመውሰድ የመጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ፤ በድምፃችን ለሀገር ዕድገት የሚበጅ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስደናል ብለዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ዘለቀ አቾ እንደተናገሩት፤ የምንፈልገውን መንግሥት መመሥረት የሚቻለው ስንመርጥ ብቻ በመሆኑ ለዚህም ተመዝግበን ካርድ መውሰድ አለብን ብለዋል። መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ በመጀመሪያው ቀን በአቅራቢያቸው በሚገኝ የምዝገባ ጣቢያ በመገኘት መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ቀደም ብሎ መመዝገብ በስተመጨረሻ አካባቢ የሚፈጠሩ ጫናዎችን ለማስቀረት ይበጃል ነው ያሉት ነዋሪው። አቶ ጥላሁን ናዶ በበኩላቸው፤ በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ለመወሰን በአምስት ዓመታት አንድ ጊዜ የሚገኝውን ዕድል ለመጠቀም እንደተዘጋጁ ገልጸዋል። ተመዝግቤ በያዝኩት ካርድ ለሀገር የሚበጅ ሃሳብ የሚያንፀባርቀውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብለዋል። ወይዘሮ ባንቻየሁ ክፍሌ የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ፤ ሁሉም ዜጋ ለምርጫው ውጤታማነት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ሀገራዊ ግዴታውን መወጣት እንዳለበት አመልክተዋል። አቶ ቶፊቅ ጃዋር በበኩላቸው፤በምርጫ መሳተፍ ከአንድ ሀገር ወዳድ ዜጋ የሚጠበቅና ዴሞክራሲያዊ መብትን የመጠቀም ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። ካርድ ወስዶ በምርጫ መሳተፍ የዘመናዊነት መገለጫ በመሆኑ በዛሬው ዕለት ተመዝግቤ ካርድ ወስጃለሁ ብለዋል።
ፖለቲካ
የትግራይ ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል -ምሁራን
Mar 8, 2026 58
ቦንጋ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ክልል ሕዝብ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ተጠቃሚነት ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ በሀገር ደረጃ እየተመዘገበ ካለው ሁሉን አቀፍ ልማትና ሰላም ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባው መግለፃቸው ይታወቃል። ለክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ልማትና ተጠቃሚነት መንግስት ቁርጠኛ አቋም ይዞ እየሰራ መሆኑን አንስተው የህወሃት ቡድን ለሌላ ጦርነት እየሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያ በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግኑኝነት ትምህርት ክፍል መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ያሬድ አያሌው (ዶ/ር)፣ የተራማጅነት እሳቤ የሌለው የህወሃት ቡድን ዘመኑን ለሚመጥን የፖለቲካ እሳቤ ዝግጁነት የሌለው መሆኑን ባለፉት ዓመታት ማየት ተችሏል ብለዋል። ይህም በመሆኑ በተለይም የትግራይ ክልልና ህዝቡ የለውጡ ተጠቃሚ እንዳይሆን መሰናክል ሆኗል ሲሉ ጠቅሰዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን ያለውን የጸና አቋም የገለጹበት መሆኑን አንስተው፣ የህወሃት ቡድን ከዚህ በተቃራኒ ቆሞ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም የህወሃትን ቡድን ያረጀ አስተሳሰብ ለመቀየር በተለይም የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ተነሳሽነት ወስዶ መንቀሳቀስ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። የህወሃት ቡድን የትግራይን ሕዝብ በተለይም ወጣቱን ሀይል እንደማሲያዣ በመጠቀም አሁን እንደሀገር እየተመዘገበ ካለው የልማት፣ የሰላምና የአንድነት ጉዞ ተነጥሎ እንዲኖር እያደረገው መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የጥፋት ቡድኑን በቃ ሊለው ይገባል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግስት የትግራይ ሕዝብ ወደ ሰላሙ እንዲመለስ እና የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጽኑ ፍላጎት እንዳለው ያሳያል ያሉት ዶክተር ያሬድ ፤ ህዝቡም የመንግስትን ጥረት ደግፎ ለለውጥ መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ የህወሃትን ቡድን እኩይ ዓላማ ማክሸፍ የሚችለው ጠንካራ ትብብርና ፅኑ ትግል ማድረግ እንዳለበት ጠቁመው፤ ይህንን ለማድረግ ጊዜ ማባከን አይገባም ብለዋል። በዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ አዲሱ ፍሪንጆ (ዶ/ር) ፤ እንዳሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክልሉ ተፈጥሮ የነበረውን የሰላም እጦት ምክንያት ለይተው ለዘላቂ ሰላም ጠቃሚ ናቸው ያሏቸውን ሃሳቦች ማንሳታቸው ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። የትኛውም የፖለቲካ አስተሳስብ ከዘመኑ ጋር ተራማጅ መሆኑን ያነሱት ምሁሩ፣ የህወሃት ቡድን ተቀባይነት በሌለውና በቆየ አስተሳሰብ ዛሬም እቀጥላለሁ ማለቱ የማይለወጥና ቆሞ ቀርነቱን ያሳያል ብለዋል። ባረጀ አስተሳሰቡ ቀደም ሲል በፈጠረው ግጭት የትግራይ ክልል ህዝብ ከልማት እንዳይጠቀም ማደረጉን አስታውሰው፣ ሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ በተለይ ወጣቱ ቡድኑን ሌላ ግጭት አንፈልግም ሊለው ይገባል ብለዋል። ወጣቶች ሁሌም ለሰላም ሊቆሙ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክትና ማብራሪያ ከትግራይ ክልል ነባራዊ ሁኔታ ባሻገር የኢትዮጵያን የፖለቲካ አካሄድና ሥርዓት ያሳየ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ቢመርቅ በርሁን ናቸው። ይህም ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸው፤ በተለይ የትግራይ ወጣቶች በአረጀ አስተሳሰብ ከተቸነከረው የህወሃት ቡድን ራሱን በማላቀቅ ለክልሉ ሰላምና የተሻለ አማራጭ መቆም እንዳለበት ገልጸዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች እያካሄዱት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት ያግዛል - ምሁራን
Mar 8, 2026 78
አሶሳ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች እያካሄዱት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እንደሚያግዝ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናገሩ። 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማከናወን የዕጩዎች ምዝገባ የተጠናቀቀ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ደግሞ የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ ይገኛል። በምርጫው ዜጎች የተሻለ ሃሳብ እና ፖሊሲ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ እንዲያስችላቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮችን እያከናወኑ መሆናቸው ይታወቃል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን እንደተናገሩት፤ ምርጫን በህገ መንግስቱ መሠረት በተያዘለት ገደብ ማከናወን አንዱ የዴሞክራሲ መገለጫ ነው። በዩኒቨርሲቲው የፌዴራሊዝም መምህር ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉት የምርጫ ቅስቀሳና የሐሳብ ክርክሮች ህብረተሰቡ ስለሚመርጠው ፓርቲ የተሻለ ግንዛቤ እንዲይዝ ያደርጋሉ ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን በነፃነት እያከናወኑት የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት የሚያግዝ እና የፓርቲዎች ማኒፌስቶ ለመራጮች ተደራሽ እንዲሆን ያግዛል ነው ያሉት። የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅሰቀሳ ወቅት የሚያነሱት የምረጡኝ ቅስቀሳ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት ያለው መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነምግባርን በማክበር በሃሳብ ብቻ መከራከርን መልመድ አለባቸው ያሉት ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ፤ ሀገርን የሚጠቅሙ ሀሳቦች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ጠቅሰዋል። ሌላው በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህር አበበ አኖ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ምርጫ ለአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች መፍትሔ ያመጣል ተብሎ ስለሚጠበቅ የዜጎችን ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው ብለዋል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዜጎች አሳሳች የሆነ አስተሳሰብ እንዳይዙ በማድረግ ግልፅ ፖሊሲና በምርጫው ቢያሸንፉ ሊፈጽሙት በሚገባው ትክክለኛ ፖሊሲ ላይ ትኩረት አድርገው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመዋል።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የምርጫ ካርዳችንን ወስደናል - የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 92
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ይጠቅመናል ያልነውን ለመምረጥ የምርጫ ካርዳችንን መውሰዳቸውን በአዲስ አበባ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያካሄድ አስታውቋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎች ማስመዝገባቸውንም መግለጹ ይታወሳል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ተጀምሯል። የኢዜአ ሪፖርተሮች በከተማዋ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች በመዘዋወር የመራጮች የምዝገባ ሂደት ቅኝት አድርገዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ዮሀንስ አሰፋ እንደተናገረው፤ ምርጫ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ የእድገትና የልማት ጉዞ የሚያሸጋግር ፓርቲ የምንመርጥበት ኹነት ነው። ስለሆነም ኢትዮጵያን በልማት ሊያሳድግና ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያደርስ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ብሏል። ዕድሜው ለመራጭነት የደረሰ ሁሉ ምርጫ ካርድ በመውሰድ በንቃት መሳተፍ እንዳለበት አመልክቷል። በጠቅላላ ምርጫ ለሀገር ይበጃል የምለውን ለመምረጥ የምርጫ ካርዱን መውሰዱን የተናገረው ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ ኤልዔዘር ደጉ ነው። ወጣቶች ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም መምረጥ እንዲችሉ ምርጫ ካርዳ እንዲወስዱም ጥሪ አቅርቧል። በጉለሌ ክፍለ ከተማ የመራጭነት ካርድ የወሰዱት አቶ ወርቁ ይርጋው በበከላቸው፤ ኢትዮጵያን ለወደፊት የሚመራና ወደ ተሻለ የዕድገት ደረጃ ሊያሻግር የሚችል ፓርቲ ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ ምርጫ ለሰላምና ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስፈላጊ በመሆኑ የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን የተናገሩት ደግሞ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ነዋሪዋ ወይዘሮ አማረች በሱፍቃድ ናቸው፡፡ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ነዋሪ ወጣት እንደሻው ነጋሽ በበኩሉ፤ በመጪው ጊዜ ለዕድገት የሚሰራ ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ካርድ በመወሰዴ ደስተኛ ነኝ ብለዋል፡፡ የዘንድሮ ምርጫ በዲጂታል የታገዘ መሆኑ ታአማኒነትን የሚጨምርና የተለያዩ መረጃ መጣረሶችን የሚያስቀር መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Mar 7, 2026 94
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተባባሪነት የተዘጋጀው ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' የተሰኘ መጽሐፍ ምረቃ መርሃ ግብር በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል። በመጽሐፉ ምረቃ መርሃ ግብር ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት፤ መጽሀፉ በሀሳብም ሆነ በይዘት የተሳካለት የታሪክ ካስማ ነው ብለዋል። በ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ላይ ታሪክ ሊይዛቸው የሚገቡ ቁምነገሮች መካተታቸውን ገልጸዋል። መጽሐፉ ታሪክ የዘነጋቸውን የዓድዋ ጀግኖች በቅጡ በመዘከር ለማስታወስ ያደረገው ጥረትም የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። የመጽሐፉ ጽንሰ ሃሳባዊ ቁምነገሮችም የኢትዮጵያዊነትን መንፈስ የሚያሰርጽ ለአዲስ ተስፋና ምኞት የሚያነሳሳ የታሪክ ሰነድ መሆኑን አንስተዋል። ''ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ዛሬን የምንሰራበትና ነገን የምንከተልበት ኃያል መነጽር መሆኑን አስረድተዋል። የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ክብር ያላቸውን ቁርጠኝነት የበየነ ዓለም አቀፍ ድል ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ መጽሐፉም የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ፋይዳ አመላክቷል ብለዋል። መጽሐፉም የዕውቀት ማስፋፊያ፣ የጎደለ መሙያ፣ ራስን መፈተሻ፣ ራስን ለመመርመር የሚያነሳሳና ምክንያታዊ እሳቤን የሚያጎለብት ሰነድ መሆኑንም ጠቁመዋል።
''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ስሁት የታሪክ አረዳድን ለማረም ትልቅ ፋይዳ አለው
Mar 7, 2026 90
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ለሕትመት መብቃቱ ስሁት የታሪክ አረዳድን ለማረም ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተባባሪነት የተዘጋጀው ''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' የተሰኘ መጽሐፍ ተመርቋል። በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተዘጋጀው የመጽሐፉ ምረቃ መርሃ ግብር ላይ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። በመጽሐፍ ላይ ምርቃት ላይ ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፣ ሀጎስ አብርሀ (ዶ/ር)፣ ደቻሳ አበበ (ዶ/ር) እና የመጽሐፉ ደራሲ አሻግሬ ገብረወልድ (ዶ/ር) ምልከታቸውን አጋርተዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፤ የዓድዋ ድል ታሪክ ቀያሪ ወታደራዊ ድል ብቻ ሳይሆን ቅኝ ግዛትን የሰበረ የነፃነት ፈር ቀዳጅ የእኩልነት ዓርማ ነው ብለዋል። ''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ለሕትመት መብቃቱም ስሁት የታሪክ አረዳድን ለማረም ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። በመጽሐፉም ቅድመ አያቶችን በዓድዋ ተራሮች የተቀዳጁትን አንጸባራቂ ድልና በርካታ ጉዳዮችን ቀለል ባለ አቀራረብ ተቀንብቦ ለተደራስያን መቅረቡን ተናግረዋል። የዓድዋ ድል ለሀገረ መንግስትና የወል ትርክት ግንባታ ወሳኝ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በመጽሐፉም የታሪክ ጉድለቶችን በመሙላት የዓድዋ ድልን ምሉዕነት በሚያሳይ መልኩ ተተርኮ ቀርቧል ብለዋል። ሌላኛው በመጽሐፉ ላይ ዳሰሳ ያቀረቡት የታሪክ ምሁር ሀጎስ አብርሀ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በመጽሐፉ የዓድዋ ድልን ከማወዳደር ይልቅ የጋራ ታሪክና የሁሉም ኢትዮጵያዊያን መሆኑን በተግባር አትቷ ብለዋል። በመጽሐፉ ላይ ተቀንብበው የቀረቡ ሃሳቦችም ለቀጣይ ጥናትና ምርምር እንዲሁም አሰባሳቢ ትርክት ግንባታን ለማጎልበት በማጣቀሻነት የሚያገለግል መሆኑን ገልጸዋል። የታሪክ ምሁር ደቻሳ አበበ (ዶ/ር)፤ በመጽሐፉ ላይ የተከተቡ ወሳኝ ጽንሰ ሃሳቦች የዓድዋ ድልን በአግባቡ በመተረክ የትውልዱን የታሪክ አረዳድ የሚቀርጽ ነው ብለዋል። ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ መጽሐፍ ደራሲ አሻግሬ ገብረወልድ (ዶ/ር)፤ የመጽሐፉ መታሰቢያነት ለኢትዮጵያ ሉዓላዊ አንድነት መስዋዕትነት ለከፈሉ ሆናል ብለዋል። በጽሐፉም የተለያዩ ሰነዶችን በማጣቀስ የዓድዋን የድል ታሪክ በቅጡ የከተበና ለአዳዲስ የታሪክ ትናትና ምርምር ሥራዎች መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ''ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን ተሻጋሪ ድል እና የወል ትውስታ'' መጽሐፍ ለስኬት እንዲበቃ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
በምርጫ ካርዳችን የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት ተዘጋጅተናል- ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 115
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦በምርጫ ካርዳችን የሚበጀንን በመምረጥ የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት ተዘጋጅተናል ሲሉ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ለስኬታማነቱ በቅንጅት እየተሠራ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ዛሬ የመራጮች ምዝገባ መጀመሩ ይታወቃል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች ፤ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ተሳትፈን ዲሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀምና የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት የመራጭነት ካርድ ወስደናል ብለዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ዘሪሁን ሎሪሶ፤ በምርጫው ሂደት የአንድ ሰው ድምጽ ትልቅ ድርሻ እንዳለው በመረዳት በመራጭነት መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ምርጫው በቀጣይ ሀገሪቱን የሚመራ ፓርቲን ወደ ስልጣን ለማምጣት ብቸኛ መንገድ በመሆኑ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀምና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት መወሰናቸውን ነው የተናገሩት። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ በመገናኛ ብዙሃን እያካሔዱ ባለው የክርክር መድረክ ፕሮግራማቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁን በመሆኑ የሚበጀንን ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስደናል ነው ያሉት። ወይዘሮ የኔዓለም ሳሙኤል በበኩላቸው፤ የምፈልገውን ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት የመራጭነት ካርድ መውሰድ የግድ በመሆኑ ወደ ምርጫ ጣቢያው በመምጣት ተመዝግቤ ካርድ ወስጃለሁ ብለዋል። ምርጫው ፍትሐዊ፣ ሰላማዊና ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻችንን ለመወጣትና ለሚበጀን የፖለቲካ ፓርቲ ድምፃችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል ሲሉም ተናግረዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አማኑኤል ፊሊጶስ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት በመገናኛ ብዙሃን የሚደረጉ ክርክሮች የተሻለ አማራጭ ያለው የፖለቲካ ፓርቲን ለመለየት የሚያስችል ነው ብለዋል። በመሆኑም የነገዋን ኢትዮጵያ መፃኢ ዕድል በምርጫ ካርዳቸው ለመወሰን በጉጉት እየተጠባበቁ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ለስኬታማነቱ በቅንጅት እየተሠራ ነው
Mar 7, 2026 76
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ለስኬታማነቱ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ። ይህ የተባለው "የዴሞክራሲ ባህልን በምርጫ መገንባት" በሚል ርዕስ በተዘጋጀ የፓናል ውይይት ላይ ነው። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል የፓናል ውይይቱ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ያለው 5ኛው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት አካል ሲሆን፥ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ እንደገለጹት፥ ምርጫ የአንድ ወቅት ተግባር ቢሆንም ሂደቱና ከምርጫው በኋላ የሚከናወኑ ተግባራት ለሀገር ግንባታ ወሳኝ ናቸው። የምርጫ ሂደቱ የሕግ የበላይነት የተረጋገጠበት፣ መቻቻልና መግባባት የሰፈነበት እንዲሆን የተጀመሩ ቅንጅታዊ አሠራሮች መጠናከር እንዳለባቸው አስረድተዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚኖረውን አዎንታዊ ሚና ማጉላት እንደሚገባ ጠቅሰው፥ ለዚህም በተቋማት መካከል የተናበበ ሥራ ወሳኝ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ንዋይ በበኩላቸው፥ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ ሰፋፊ የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። የምርጫ መርኃ ግብሩ በጊዜ ሰሌዳው መሠረት እንዲፈጸም ቦርዱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል። እስካሁን ባለው ሂደት የእጩዎች ምዝገባ ተደራሽነትን ባረጋገጠ መልኩ መጠናቀቁንና ለመራጮች ምዝገባም የተለያዩ አማራጮች መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። በተጨማሪም የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሀሳቦቻቸውን በመገናኛ ብዙኃን የሚያስተዋውቁበት ምቹ የሥራ ምኅዳር መፈጠሩን በማንሳት፥ ይህም የዴሞክራሲ ባህል እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ እንዳሉት፤ በምርጫው ሂደት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የነቃ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በትኩረት እየተሠራ ነው። ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ድርጅቶቹ ያላቸውን ሚና እንዲያጎለብቱ የተለያዩ ሥርዓቶች መዘርጋታቸውን በመግለፅ፥ ባለሥልጣኑ ለዚህ የሚረዳ ራሱን የቻለ ዕቅድ አውጥቶ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አስረድተዋል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አሕመድ ሁሴን በበኩላቸው፥ ሕዝቡ በምርጫው ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ለማስገንዘብ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። ምርጫ ዜጎች ተወካዮቻቸውንና መሪዎቻቸውን በድምፃቸው በመምረጥ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን እውን መሆን የሚያረጋግጥና ለሀገር ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አበራ ኃይለማርያም፥ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታዛቢዎችን ቁጥር በላቀ ሁኔታ ከፍ ለማድረግ ጥረት መደረጉን ገልጸዋል። በተለይም የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውንና ሂደቱ ፍትሐዊና ተአማኒ እንዲሆን የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት ላይ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።
ሁሉም ዜጋ በምርጫው የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ሀገራዊ ግዴታውን መወጣት ይኖርበታል-የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች
Mar 7, 2026 159
ሚዛን አማን፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፡- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ዜጋ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ሀገራዊ ግዴታውን መወጣት ይኖርበታል ሲሉ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መራጮች የምርጫ ካርድ መውሰድ ጀምረዋል በግንቦት ወር ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ መጀመሩ ይታወቃል። ኢዜአ በሚዛን አማን ከተማ በተደራጁ የምርጫ ጣቢያዎች በመዘዋወር ካርድ ለመውሰድ ወደ ጣቢያዎቹ ያቀኑ መራጮችን አነጋግሯል። ተመዝግበው ካርድ ለመውሰድ የመጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ፤ በድምፃችን ለሀገር ዕድገት የሚበጅ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስደናል ብለዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ዘለቀ አቾ እንደተናገሩት፤ የምንፈልገውን መንግሥት መመሥረት የሚቻለው ስንመርጥ ብቻ በመሆኑ ለዚህም ተመዝግበን ካርድ መውሰድ አለብን ብለዋል። መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ በመጀመሪያው ቀን በአቅራቢያቸው በሚገኝ የምዝገባ ጣቢያ በመገኘት መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ቀደም ብሎ መመዝገብ በስተመጨረሻ አካባቢ የሚፈጠሩ ጫናዎችን ለማስቀረት ይበጃል ነው ያሉት ነዋሪው። አቶ ጥላሁን ናዶ በበኩላቸው፤ በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ለመወሰን በአምስት ዓመታት አንድ ጊዜ የሚገኝውን ዕድል ለመጠቀም እንደተዘጋጁ ገልጸዋል። ተመዝግቤ በያዝኩት ካርድ ለሀገር የሚበጅ ሃሳብ የሚያንፀባርቀውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብለዋል። ወይዘሮ ባንቻየሁ ክፍሌ የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ፤ ሁሉም ዜጋ ለምርጫው ውጤታማነት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ሀገራዊ ግዴታውን መወጣት እንዳለበት አመልክተዋል። አቶ ቶፊቅ ጃዋር በበኩላቸው፤በምርጫ መሳተፍ ከአንድ ሀገር ወዳድ ዜጋ የሚጠበቅና ዴሞክራሲያዊ መብትን የመጠቀም ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። ካርድ ወስዶ በምርጫ መሳተፍ የዘመናዊነት መገለጫ በመሆኑ በዛሬው ዕለት ተመዝግቤ ካርድ ወስጃለሁ ብለዋል።
ማህበራዊ
መንግሥት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ ነው
Mar 8, 2026 6
ጅግጅጋ፣ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ መንግሥት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል የሴቶች እና ህጻናት ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኡበህ አብዱረህማን ተናገሩ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8) "50ኛ ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ተከበረ። የሶማሌ ክልል የሴቶች እና ህጻናት ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኡበህ አብዱረህማን እንደገለጹት፣ መንግሥት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ ነው። የሴቶችን ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሠሩ ሥራዎች አበረታች ለውጦች መገኘታቸውንም ነው የተናገሩት። በሶማሌ ክልል ሴቶችን ለአመራርነትና ውሳኔ ሰጪነት በማብቃት በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ የላቀ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል። ባለፉት አመታት የተገኙትን የሴቶች ተሳትፎ የሚያጠናክሩ ስኬቶች ማስቀጠልና ማጎልበት እንደሚገባም ተናግረዋል። ያለ ሴቶች ንቁ ተሳትፎ ኢትዮጵያ ያቀደችውን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ የማይታሰብ መሆኑን አንስተው በዚህ ረገድ ጠንካራ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል ዘሀራ ዩሱፍ ሴቶች የቤተሰብና የህብረተሰብ ምሰሶ እንደሆኑ ተናግረው እናቶች አምራች ትውልድ በማፍራት የሀገር ባለውለታ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሴቶች መንግሥት እያከናወነ ያለውን ልማት በመደገፍ የድርሻቸውን እንዲወጡ ለይላ ሂስ አህመድ ጠየቀዋል፡፡
የሥርዓተ ጾታ እኩልነትንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)
Mar 8, 2026 26
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የሥርዓተ ጾታ እኩልነትንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ወደ ሀገር ውስጥና ውጭ ሀገራት በሴቶች ብቻ የሚመሩ ስምንት በረራዎች እንደሚከናወን አስታውቋል፡፡ ሚኒስትሯ ይህንን የገለጹት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (ማርች ምክንያት በማድረግ በሴቶች ብቻ ለሚመራው የበረራ ቡድን በስካይላይት ሆቴል በተዘጋጀው የሽኝት መርሃ ግብር ላይ ነው። አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት በሴቶች የሚመሩ ስምንት በረራዎችን ያደርጋል። በዚህ ወቅት የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ አየር መንገዱ የኢትዮጵያ ኩራት በመሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሀገርን ስም ከማስጠራት ባለፈ፣ ሴቶችን በማብቃት ረገድ አርዓያነት ያለው ተግባር እያከናወነ ይገኛል። አየር መንገዱ የጾታ እኩልነትን፣ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሴቶችን ለማብቃትና እኩል ዕድል ለመፍጠር የግሉ ዘርፍም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል። መንግስት ሴቶች ሙሉ አቅማቸውን እንዲያወጡ የሚያስችል ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ መሆኑን ጠቁመው፤ የስርዓተ ፆታ እኩልነትና የሴቶችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሴቶች ተቋም የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ጃኔት ኪም በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሴቶች ብቻ የተመራ በረራ ማድረጉ ሴቶች ዕድሉ ከተሰጣቸው የማይወጡት አቅም እንደሌለ ማሳያ ነው ብለዋል። አየር መንገዱ በአቪዬሽን ዘርፍ እያከናወነ ካለው የላቀ ተግባር በተጨማሪ ሴቶችን በዘርፉ ለማብቃት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የእኩልነት መርህን በተግባር ለዓለም ያሳየ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፤ የበረራ መርሃ ግብሩ ከፓይለት እስከ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪነት ያለውን ሂደት ጨምሮ ሙሉ በሙሉ በሴቶች የሚመራ መሆኑን ገልጸዋል። አየር መንገዱ ላለፉት ተከታታይ ዓመታት በተመረጡ ሀገራት በሴቶች ብቻ የተመራ በረራ ሲያካሂድ መቆየቱን አስታውሰው፤ ዘንድሮም ወደ ሀገር ውስጥና ውጭ ሀገራት ስምንት በረራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአየር መንገዱ 40 በመቶ ሰራተኞች እንዲሁም 35 በመቶ አመራሮች ሴቶች ሲሆኑ የሴት ፓይለቶች ቁጥርም 95 ደርሷል። ይህ የበረራ መርሃ ግብር ሴቶች በአቪዬሽን ዘርፉ ያላቸውን ተሳትፎ ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም ተመላክቷል።
የሴቶችን አቅም ለማጎልበትና ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ ለማረጋገጥ ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል - ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር)
Mar 7, 2026 120
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ የሴቶችን አቅም ለማጎልበትና ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ ለማረጋገጥ ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን(ማርች 8 ) ምክንያት በማድረግ በሴቶች ብቻ ለሚመራው የበረራ ቡድን በስካይላይት ሆቴል ሽኝት ተደርጓል። አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት ከዛሬ ምሽት ጀምሮ በሴቶች የሚመሩ ስምንት በረራዎችን ያደርጋል። በዚሁ መርሃ ግብር የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) የሴቶችን አቅም ለማጎልበትና ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ ለማረጋገጥ ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። አየር መንገዱ የኢትዮጵያ ኩራት በመሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሀገርን ስም ከማስጠራት ባለፈ፣ ሴቶችን በማብቃት ረገድ አርአያነት ያለው ተግባር እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። አየር መንገዱ የጾታ እኩልነትን፣ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሴቶችን ለማብቃትና እኩል ዕድል ለመፍጠር የግሉ ዘርፍም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሴቶች ተቋም የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ጃኔት ኪም በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሴቶች ብቻ የተመራ በረራ ማድረጉ ሴቶች ዕድሉ ከተሰጣቸው የማይወጡት እንደሌለ ማሳያ ነው ሲሉ ገልጸዋል። አየር መንገዱ በአቪዬሽን ዘርፍ እያከናወነ ካለው የላቀ ተግባር በተጨማሪ ሴቶችን በዘርፉ ለማብቃት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የእኩልነት መርህን በተግባር ለዓለም ያሳየ ተግባር ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ የበረራ መርሃ ግብሩ ከፓይለት እስከ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪነት ያለውን ሂደት ጨምሮ ሙሉ በሙሉ በሴቶች የሚመራ መሆኑን ገልጸዋል። አየር መንገዱ ላለፉት ተከታታይ ዓመታት በተመረጡ ሀገራት በሴቶች ብቻ የተመራ በረራ ሲያካሂድ መቆየቱን አስታውሰው፤ ዘንድሮም ወደ ጅቡቲ፣ ናይሮቢ፣ ፍራንክፈርትና ድሬዳዋን ጨምሮ ስምንት በረራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የአየር መንገዱ 40 በመቶ ሰራተኞች እንዲሁም 35 በመቶ አመራሮች ሴቶች ሲሆኑ የሴት ፓይለቶች ቁጥርም 95 ደርሷል ሲሉ ገልጸዋል። ይህ የበረራ መርሃ ግብር ሴቶች በአቪዬሽን ዘርፉ ያላቸውን ተሳትፎ ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም ተመላክቷል። በሽኝት መርሃ ግብሩ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ሴት አብራሪዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ሙስሊሙ ማህበረሰብ የረመዳን ወርን የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳትና በመደጋገፍ ሊያሳልፈው ይገባል
Mar 7, 2026 74
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ሙስሊሙ ማህበረሰብ የረመዳን ወርን የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳትና በመደጋገፍ ሊያሳልፈው እንደሚገባ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ገለጹ፡፡ “ነጃሺ ለሀገር” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው 6ኛው ታላቁ የጎዳና ላይ የኢፍጣር መርሃ-ግብር በአዲስ አበባ ከተማ ተካሂዷል። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ዑስታዞች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ተጋባዥ እንግዶች እና የእስልምና እምነት ተከታዮች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ታላቁን የጎዳና ላይ ኢፍጣር በዚህ መልኩ በጋራ ማከናወን መቻሉ እጅግ የሚያስደስት ነው ብለዋል፡፡ ይህ መድረክ የሙስሊሙ ማህበረሰብ አንድነት ከቃል ባለፈ በተግባር የታየበት መሆኑ ተናግረዋል፡፡ ወጣቶች ኃላፊነቱን ወስደው መርሃ-ግብሩን ማዘጋጀታቸው የሚደነቅ ነው ያሉት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ወጣቶች ለአንድ ዓላማ ቆመው በማየቴ ትልቅ ደስታ ተሰምቶኛል ብለዋል። ረመዳን የተቸገሩ ወገኖች የሚረዱበት ወር መሆኑን አስታውሰው ምዕመኑ በረመዳን ወር ማዕድ በማጋራት ችግረኞችን መደገፍ ይጠበቅባቸዋል ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይኽ መሐመድ ሸሪፍ ሃሰን በበኩላቸው፤ በረመዳን አብሮነትንና መረዳዳትን ማጎልበት ይገባል ብለዋል፡፡
ኢኮኖሚ
በክልሉ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው
Mar 7, 2026 71
ሀዋሳ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ላደረጉ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም ተካሄዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው። የክልሉ መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ስራ አጥ ዜጎችን ወደ ስራ ለማስገባት በሚደረገው ጥረት በክልሉ የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የፋይናንስና የክህሎት ስልጠና በመስጠት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የክልሉ መንግስት ከአጋር አካላት ጋር የጀመረውን ቅንጅት በማጠናከር በዘርፉ የሚከናወነውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ በበኩላቸው፤ በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ዘርፍ ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን በመተግበር ሂደት የክህሎት ልማት ላይ የተከናወኑ ተግባራት በዘርፉ ለተገኘው ውጤት ጉልህ ሚናን አበርክቷል ብለዋል። የስራ እድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ኢንዱስትሪውን እንዲቀላቀሉ በሚደረገው ጥረት የማምረቻና መሸጫ ቦታዎችን በማዘጋጀትና የማሽነሪ ድጋፍ መደረጉንም ተናግረዋል። የዛሬው መድረክ ዋና ዓላማም እስካሁን ለተከናወነው ተግባር ምስጋና በማቅረብ በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት ቅንጅቱን የማጠናከር ስራ ለመስራት ነው ብለዋል። በክልሉ የሚንቀሳቀሱ አጋር አካላት በተያዘው በጀት ዓመት ከ39 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስልጠና ድጋፍ ማድረጋቸውም ታውቋል።
በዞኑ ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ናቸው
Mar 7, 2026 113
ሆሳዕና ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በከምባታ ዞን ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ ፕሮጀክቶች የነበሩባቸውን ችግሮች በመቅረፍ ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድጉ መሆኑን የዞኑ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበልግ ወቅት ከ208 ሺህ 602 ሄክታር በላይ መሬት ይለማል የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በከምባታ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች የመስኖ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድና የተንጠልጣይ ድልድይ ፕሮጀክቶችን ግንባታ አጠናቆ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል፡፡ የዞኑ ነዋሪዎች በዚህ ወቅት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉ ፕሮጀክቶች የነበሩባቸውን ችግሮች በመቅረፍ ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡ በዞኑ የሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር በለጠ ሾቢሶ፤ በአካባቢያቸው ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የሳቶራ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው በመስኖ ልማት እንዲሳተፉ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ከመደበኛ የግብርና ስራቸው በተጨማሪ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በወቅት ሳይገደቡ አልምተው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያሳድግም ገልጸዋል፡፡ በቃጫቢራ ወረዳ መሳፌ ቀበሌ ነዋሪው አርሶ አደር አስፋው አንሼቦ በበኩላቸው፤ በአካባቢያቸው የመንገድ መሰረተ ልማት ባለመኖሩ የሚያመርቱትን ምርት ለገበያ ለማቅረብም ሆነ ማህበራዊ አገልግሎት ለማግኘት ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ የክልሉ መንግስት ያጠናቀቀው መንገድ የጤና አገልግሎትን ጨምሮ የግብርና ምርታቸውን በቀላሉ ወደ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንደሚያደርጋቸውም ተናግረዋል፡፡ በአካባቢው የንፁህ ውጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በመኖሩ ከወራጅ ወንዝ በመጠቀም ለተላላፊ በሽታዎች ይጋለጡ እንደነበር የገለጹት ደግሞ በዞኑ የዶዮገና ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘሮ ብዙነሽ ኃይለ ማርያም ናቸው፡፡ በአካባቢው ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም የነበረባቸውን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት ሙሉ በሙሉ የሚቀርፍ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ እንደገለፁት፤ በክልሉ መንግስት የተገነቡት የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የመስኖ፣ የመንገድና የተንጠልጣይ ድልድይ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡ የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረግ የዞኑ ማህበረሰብ በሁሉም ዘርፍ ያለውን አቅም እንዲጠቀምና ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችለው ስለመሆኑም አመልክተዋል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በቅርቡ የተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡
የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማፋጠን አዳዲስ የምርምር ሥራዎች እየተካሄዱ ነው
Mar 7, 2026 113
አምቦ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማፋጠን አዳዲስ የምርምር ሥራዎችን እያካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለጸ። በክልሉ በቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመስኖ ልማት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ኢንስቲትዩቱ በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል የተሻሻሉ የወተት ላሞች ዝርያን ለሞዴል አርሶ አደሮች የማስተላለፍ እና የዕፅዋት ጥበቃ ምርምር ቤተ-ሙከራ ቁሳቁሶች የርክክብ ሥነ-ሥርዓት አካሂዷል። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ንጉሤ ደቻሳ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢንስቲትዩቱ የግብርናውን ዘርፍ ይበልጥ ለማዘመን የተለያዩ አዳዲስ የምርምር ሥራዎችን እያካሄደ ይገኛል። የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባለፈ፣ የሀገሪቱን እድገት ማፋጠን የሚችሉ በሳይንሳዊ ምርምር የተደገፉ ዘርፈ-ብዙ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለአብነትም በባዮ-ቴክኖሎጂ ሥራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር መደረጉን ገልጸዋል። በቀጣይም የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለማፋጠን የሚያግዙ አዳዲስ የምርምር ሥራዎች በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥሉ መሆኑን አንስተዋል። የአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ጃማል ቶላ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የምርምር ማዕከሉ የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር መፍታት የሚችሉ የተለያዩ የግብርና ምርምር ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ጠቅሰዋል። ከተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) ድጋፍ የተገኘ የዕፅዋት ጥበቃ ምርምር ቤተ-ሙከራ ቁሳቁሶችን ኢንስቲትዩቱ ለአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ማስረከቡንም አስታውሰዋል። የቤተ-ሙከራ ቁሳቁሶቹ የዕፅዋት በሽታዎችን ለመለየትና የአካባቢውን አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚረዱ ተናግረዋል። ለብዙ ዓመታት የምርምርና ብዜት ሥራ ሲከናወንባቸው የነበሩ የተሻሻሉ የወተት ላሞች ለሞዴል አርሶ አደሮች ተላልፈው መሰጠታቸውን የተናገሩት ደግሞ በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል የጊንጪ መለስተኛ ግብርና ማዕከል ዳይሬክተር ተስፋዬ አበራ (ዶ/ር) ናቸው። ማዕከሉ የወተት ላሞቹን ካስተላለፈ በኋላም አርሶ አደሮቹን በአንድ መንደር በማደራጀት አስፈላጊውን ሙያዊ ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እንደሚሠራም ገልጸዋል። የአካባቢው አርሶ አደሮችም የተሻሻሉ የወተት ላሞች ዝርያ በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው፤ ለላሞቹ አስፈላጊውን ጥበቃ በማድረግ ገቢያቸውን ለማሻሻልና በሀገራዊ እድገት ውስጥ ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የአምቦ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር አቶ ወልደሰማያት ለታ፤ ከግብርና ሥራቸው ጎን ለጎን የወተት ላሞቹን በማርባት ከሚያገኙት ምርት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ገቢያቸውን ለማሳደግ እንደሚሠሩ ተናግረዋል።
የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎች እየተዘረጉ ነው
Mar 7, 2026 172
አዳማ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በዘላቂነት ለመጠበቅና የዘርፉን አሰራር ለማዘመን የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎችን እየዘረጋ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ገለጸ። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና የኢትዮጵያን የንግድ ምህዳር ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታላቅ ዕድል ነው ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የረቂቅ ደንቡን ይዘት በባለድርሻ አካላት ግብዓት ለማዳበር ያለመ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል። የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በህግ ለመደገፍ አዋጅ ቁጥር 1376/2018 ወጥቶ ወደ ሥራ እንዲገባ ተደርጓል። ይህም የሀገሪቱን የእንስሳትና የእንስሳት ውጤቶች የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳለጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው አሰራር ለመዘርጋት ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል። አምባሳደር ድሪባ አክለውም፤ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና ምርቱን የሚረከቡ ሀገራት የሚቀበሏቸው የህግ ማዕቀፎች ተዘጋጅተዋል ብለዋል። አሁን ላይ በእፅዋትና በእንስሳት ዘርፎች አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ስታንዳርዶች ፀድቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የህግ ማዕቀፎቹ የዘርፉ ኢንዱስትሪዎች፣ በተለይም የስጋ አምራቾች ፍላጎትን መሰረት ያደረጉና ከዓለም አቀፍ አሰራር ጋር የተናበቡ እንዲሆኑ ታስቦ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የባለሥልጣኑ የሬጉላቶሪ ዘርፍ ዳይሬክተር ሃሚድ ጀማል (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባለፉት ሰባት ወራት የእንስሳት ምርት ለማምረት ፈቃድ የተሰጣቸውን ተቋማት ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የአሰራር ማሻሻያዎች መደረጋቸውን ገልጸዋል። ምርት ወደ ውጭ ከመላኩ በፊት ከማምረቻው ጀምሮ ጥራትና ደህንነቱ መጠበቅ እንዳለበት ያመለከቱት ዳይሬክተሩ፤ ምርት በቁምም ሆነ ታርዶ ለተጠቃሚው ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ እንዲላክ ተቋሙ ከግብርና ሚኒስቴርና ከባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የባለሥልጣኑ የእንስሳት ምርት ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አያሌው ሹመት በበኩላቸው፤ የህግ ማዕቀፎቹ የኤክስፖርት ዘርፉን ማነቆዎች የሚቀርፉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ይህም የቁም እንስሳት፣ ስጋ፣ ዶሮ፣ እንቁላል፣ ዓሣ፣ ወተትና የማር ምርቶችን የቁጥጥር አሰራር የሚያዘምን መሆኑን ጠቅሰዋል። በህግ ማዕቀፎቹ ዝግጅት ወቅት የዓለም ንግድ ድርጅትን ጨምሮ የናሚቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ፣ ቦትስዋና፣ እንግሊዝና የብራዚል ምርጥ ተሞክሮዎች እንዲካተቱ አድርገናል ሲሉም ገልጸዋል። የህግ ማዕቀፎቹ ተግባራዊ መሆን ለሀገሪቱ የወጭ ንግድ ውጤታማነት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረውም ተመላክቷል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በክልሉ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆችን ወደ ዲጂታል የትምህርት ስርአት ለማሸጋገር የሪፎርም ስራዎች እየተካሄዱ ነው
Mar 7, 2026 56
ጎንደር፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል አሥር የመንግሥት የመምህራን ትምህርት ኮሌጆችን ወደ ዲጂታል የመማር ማስተማር ሂደት ለማሸጋገር የሪፎርም ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡ በክልሉ ኮሌጆች ከስልጠና በተጨማሪ ለቴክኖሎጂና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ቢሮው በክልሉ የሚገኙ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች በትምህርት ጥራትና በተማሪዎች ማብቃት ዙሪያ ያከናወኗቸውን ተግባራት የሚገመግም መድረክ በጎንደር ከተማ እያካሄደ ነው፡፡ በመድረኩ የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ደምስ እድሪስ እንደተናገሩት፤ በክልሉ የሚገኙ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች በእውቀትና በክህሎት የበቁ እጩ መምህራንን ማፍራት እንዲችሉ የሪፎርም ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ የትምህርት ኮሌጆቹ ዘመኑን የዋጀ የመማር ማስተማር ሂደትን ማከናወን እንዲችሉ፣ በተካሄዱ የሪፎርም ሥራዎች የተማሪዎችን ውጤትና የምዝገባ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ስድስት የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች የቤተ-መጻሕፍት አገልግሎታቸውን ወደ ዲጂታል የአሠራር ሥርዓት መቀየር መቻላቸውን ጠቁመው፤ በቀጣይም ሁሉንም አገልግሎታቸውን ዲጂታል የማድረግ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል፡፡ የትምህርት ሥርዓቱን ውጤታማ ማድረግ፣ ጥራት ያላቸውና የበቁ መምህራንን ማፍራት እንዲሁም ሥርዓተ-ትምህርቱን በጥናትና ምርምር ማገዝ የሪፎርሙ ዋና የተልዕኮ አካል ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኮሌጆቹ በአንደኛና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተመድበው ማስተማር የሚችሉና በላቀ እውቀትና ክህሎት የሰለጠኑ መምህራን ማፍራት እንዲችሉም ሰፊ ድጋፍ እየተደረገላቸው ነው ብለዋል፡፡ ኮሌጆቹ የክልሉን የመምህራን ፍላጎት መሠረት በማድረግ በአሁኑ ወቅት በዲፕሎማና በዲግሪ መርሃ ግብር ከ10 ሺህ በላይ እጩዎችን በመምህርነት ሙያ እያሰለጠኑ እንደሚገኝም አስረድተዋል፡፡ የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ዲን አቶ የሻምበል ፀሐይ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ከተመሠረተ 44 ዓመታት ያስቆጠረው ኮሌጁ ከ64 ሺህ በላይ መምህራንን አሰልጥኖ በማስመረቅ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ የድርሻውን አበርክቷል፡፡ ኮሌጁ በዘንድሮ ዓመት በመደበኛውና በማታው የትምህርት ክፍለ ጊዜ በዲፕሎማና በዲግሪ መርሃ ግብር ከ3 ሺህ 400 በላይ መምህራን እያሰለጠነ መሆኑን ጠቁመው፣ የተማሪዎችን የምዝገባ ሥርዓት ወደ ዲጂታል ማሸጋገር መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት የበቃ ውጤታማ ትውልድ ለማፍራት የመምህራን የሥልጠና ሥርዓት ዘመኑን በዋጀ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መመራት አለበት ያሉት ደግሞ የደብረ ብርሃን መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ዲን መባ ፈጠነ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ ኮሌጁ ከተመሠረተ አንሥቶ ከ60 ሺህ በላይ የአንደኛ ደረጃ መምህራንን አሰልጥኖ ማሰማራቱን ጠቁመው፣ አሁን ላይ የመማር ማስተማር ሥራውን ዲጂታላይዝ ማድረግ የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ ለሁለት ቀናት በሚቆየው የግምገማ መድረክ ላይ ከክልሉ 10 ኮሌጆች የተውጣጡ ዲኖችና የትምህርት አመራሮችን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ታስተናግዳለች
Mar 7, 2026 74
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ(ASMIS) ልታስተናግድ ነው። ጉባኤውን የሚያዘጋጁት ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ (POA) እና ኤ.ጂ.ኤ ቴክ (AGA-Tech) ኢንተርፕራይዝ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። ጉባኤው እ.አ.አ ግንቦት 7 እና 8 ቀን 2026 በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል። የመጀመሪያ የሆነው ይህ ጉባኤ የአፍሪካ ተፅዕኖ ፈጣሪ ድምፆችን ከመገናኛ ብዙኅን ድርጅቶች፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የግሉ ዘርፍ መሪዎች ጋር የሚያገናኝ ታሪካዊ የጋራ መድረክ መሆኑ ተገልጿል። ''ተፅዕኖ ለተሻለች አፍሪካ'' በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው ጉባኤው የዲጂታል ተሳትፎ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂና ኃላፊነት ላይ ምክክር የሚደረግበት ወሳኝ መድረክ እንደሚሆንም ይጠበቃል። የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ አስተባባሪ በረከት ሲሳይ እንደገለጹት፤ ጉባኤው ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ባለው ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ የአፍሪካን የዲጂታል ገጽታና ይዘት ፈጠራ ላይ ትኩረት ያደርጋል ብለዋል። በጉባኤ የቴክኖሎጂ ሥነ-ምኅዳር ፈጠራ፣ የአፍሪካ ታሪክና መፃኢ ተስፋዎች ላይ ጥራት ያላቸው የይዘት ሥራዎችን ለማስተጋባት አቅም የሚፈጠር አህጉራዊ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ሁነቱ በአፍሪካ ሀገራትና በዓለም ዙሪያ የሚሰሩ ከ200 በላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ የማህበራዊ ሚዲያ ግለሰቦች ተሰባስበው የሚመክሩበት መሆኑንም ተናግረዋል። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦቹ በዘላቂ ልማት፣ ዲጂታል አስተዳደርና የይዘት ፈጠራ አቅምን የሚያጎለብቱ የምክክርና የትውውቅ መርሃ ግብሮች እንደሚያካሄዱ አብራርተዋል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት ልምድና ተሞክሮ የሚለዋወጡበት፣ የአፍሪካን ዕድገት በዲጂታል ሥርዓት መግለጥ የሚያስችል እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጠሪዎችን ከትላልቅ የንግድ ድርጅቶች ጋር የሚያገናኝ መድረክ መሆኑንም አንስተዋል። የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ፕሮጀክት አስተባባሪ ባዩሽ ማሞ በበኩላቸው፤፤ ጉባኤው እያደገ በመጣው የዲጂታል ዓለም የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር ትብብርና ተወዳዳሪነት ለማጎልበት አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ የሚካሄደው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ይፋዊ ምዝገባ በቅርቡ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። በዚህም የይዘት ፈጣሪዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችና ባለድርሻ አካላት ጉባኤውን የሚመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት በ www.asmis.org ድረ-ገጽን መከታተል እንደሚችሉ ገልጸዋል። የአህጉሪቱን ዲጂታል መጻኢ የፈጠራ አቅምና እጣ ፈንታ በተሻለ ይዘት ለመቅረጽ ጉባአው ወሳኝ መሆኑን ተናግረው ታላላቅ የንግድ ተቋማትና ድርጅቶችም ለጉባኤው ስኬታማነት በአጋርነት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ የአፍሪካ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፎረምን ታስተናግዳለች
Mar 7, 2026 106
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ስምንተኛው የአፍሪካ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፎረም ሚያዚያ 18 እና 19 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ያዘጋጀው ፎረም “ አጀንዳ 2030 እና አጀንዳ 2063ን በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ዲጂታል ኢኖሼሽን ውጤታማ ማድረግ” በሚል መሪ ሀሳብ ይካሄዳል። ፎረሙ የአፍሪካ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ኢኖቬተሮች እና የልማት አጋሮች በአንድ መድረክ ያገናኛል። ባለድርሻ አካላቱ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያለውን ሚና አስመልክቶ በፎረሙ ይመክራሉ። መድረኩ የአፍሪካ የኢኖቬሽን አጀንዳን የበለጠ ለማራመድ የሚያስችል ቁልፍ ማዕቀፍ ሆኖ እንደሚያገለግልም ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በመንግስት፣ በአካዳሚክ ማህበረሰቡ፣ በኢንዱስትሪ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ውይይት ይደረጋል። ፎረሙ አፍሪካ በዘላቂ ልማት ግቦች የደረሰችበትን የአፈጻጸም ደረጃ ይገመግማል። ውሃ እና ንጽህና፣ ተመጣጣኝ እና ንጹህ ኢነርጂ፣ ኢንዱስትሪ እና መሰረተ ልማት፣ ዘላቂ ከተሞችና የልማት አጋርነት ጨምሮ የተለያዩ የዘላቂ ልማት ግቦችን የተመለከተ ውይይት ይካሄዳል። የውይይቱ ተሳታፊዎች ኢኖቬሽን ተኮር መፍትሄዎች እና ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር የሚያስችሉ የተግባር እርምጃዎች ላይ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። በፎረሙ ላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ ከፍተኛ አዎንታዊ ለውጥ ያመጡ ቴክኖሎጂዎች፣ ጀማሪ የስራ ፈጠራዎች (Startups)፣ የምርምር ኢኒሼቲቮች እና የኢኖቬሽን ማዕከላት ስራዎች ለእይታ ይቀርባሉ። ኹነቱ የእውቀት ሽግግርን ለማሳለጥ፣ በዩኒቨርሲቲዎች እና ምርምር ተቋማት መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር እንዲሁም በአፍሪካ ያለውን የቴክኖሎጂ ሽግግር የመደገፍ አላማ አለው። በፎረሙ ላይ የአፍሪካ ሀገራት መንግስታት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አመራሮች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፎረም ውጤቶች በአዲስ አበባ የሚካሄደውን 12ኛው የአፍሪካ ቀጣናዊ የዘላቂ ልማት ፎረም የሚደግፉ መሆናቸው ተመላክቷል። 12ኛው የአፍሪካ ቀጣናዊ የዘላቂ ልማት ፎረም ከሚያዚያ 20 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
ኢንስቲትዩቱ የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ ምርምሮችን እያከናወነ ነው
Mar 6, 2026 167
አዳማ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ የጥናትና ምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ አስራት እንደገለጹት፤ ተቋሙ በኦሮሞ ባህል፣ እሴት፣ ስነ-ጥበብ፣ ታሪክ፣ ቋንቋና እድገት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። ወጣቶች መልካም ስብዕናን ተላብሰው ለሀገር ልማት እና እድገት እንዲተጉ የባለድርሻ አካላት ሚና ሊጠናከር ይገባል ይህንንም ውጤታማ ለማድረግ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ከሚገኙ ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ከቱሪዝም ኮሚሽን፣ ከባህል ጥናት ማዕከል እንዲሁም ከወጣቶችና ስፖርት ቢሮዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ እስካሁን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ከ70 በላይ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ከእነዚህም መካከል በታሪክ፣ በቋንቋና በባህል ላይ ያተኮሩ ከ30 በላይ መጻሕፍት ታትመው ለማህበረሰቡ ተደራሽ ሆነዋል ብለዋል። እነዚህ ስራዎች በተለይም የወጣቶችን የማንበብ ባህል ለማጠናከርና ሁለንተናዊ ስብዕናቸው እንዲገነባ ለማስቻል ትልቅ ድርሻ እንዳላቸውም አመልክተዋል። የጥናት ውጤቶቹንና የመጻሕፍት ዝግጅቱን አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች፣ ስራው በትውልዱ ላይ የሚታየውን የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላት እንደሚረዳ ገልጸዋል። ወጣት ስራጅ አህመድ እንደገለጸው፣ ንባብ ወጣቶች ስለ ማህበረሰቡ ስብዕናና ባህል እንዲያውቁ ያደርጋል። የገዳ ስርዓት መሰረታችንና ማንነታችን ነው ያለው ወጣት ስራጅ፣ ስለ ስርዓቱና ስለ ኦሮሞ እሴቶች በቂ እውቀት ለማግኘት የንባብ ባህላችንን ማጎልበት ይገባናል ብሏል። ተተኪው ትውልድ ስራን ከመናቅ ወጥቶ በልማት ስራዎች ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለበትም ነው የገለጸው።
ስፖርት
246ኛው የሚላን ደርቢ
Mar 8, 2026 44
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ) ፦ በጣልያን ሴሪአ የ28ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኤሲ ሚላን እና ኢንተር ሚላን የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ጨዋታው በሳንሲሮ ስታዲየም ምሽት 4 ሰዓት ከ45 ላይ ይካሄዳል። ኤሲ ሚላን በውድድር ዓመቱ 27 ጨዋታዎችን አከናውኖ በ16ቱ ድል ሲቀናው ሁለት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ ዘጠኝ ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 43 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 20 ግቦች ተቆጥረውበታል። ሚላን በ57 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። የከተማ ተቀናቃኙ ኢንተር ሚላን በሊጉ ካደረጋቸው 27 ጨዋታዎች መካከል 22 ጊዜ ሲያሸንፍ አራት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 64 ግቦችን ሲያስቆጥር 21 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ67 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ቡድኖች በሁሉም ውድድሮች ሲገናኙ የአሁኑ ለ246ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 245 ጨዋታዎች ኢንተር ሚላን 91 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። ኤሲ ሚላን 83 ጊዜ ሲያሸንፍ በቀሪዎቹ 71 ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። በሴሪአው 183 ጊዜ ተገናኝተው ኢንተር ሚላን 70፣ ኤሲ ሚላን 56 ጊዜ አሸንፈዋል። 57 ጊዜ ነጥብ ተጋርተዋል። ባለፉት 10 የሴሪአ ግንኙነታቸው ሁለቱም በተመሳሳይ አራት ጊዜ አሸንፈዋል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። በዘንድሮው የውድድር ዓመት በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ኤሲ ሚላን በክርስቲያን ፑሊሲች ጎል 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ክለቦቹ ለ117 ዓመታት የዘለቀ ተቀናቃኝነት አላቸው። ኢንተር ሚላን 20 እና ኤሲ ሚላን 19 ጊዜ የሴሪአ ዋንጫን አንስተዋል። በአህጉራዊ መድረክም ኤሲ ሚላን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግን ሰባት ጊዜ በማንሳት ስኬታማው ክለብ ነው። ኢንተር ሚላን ሶስት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ሆኗል። በውድድር ዓመቱ ጠንካራ ፉክክር እያደረጉ የሚገኙት ክለቦች የሴሪአ ጨዋታ የተመልካቾችን ቀልብ ስቧል። ኢንተር ሚላን ካሸነፈ የሊጉን መሪነት ያጠናክራል። በአንጻሩ ኤሲ ሚላን ድል ከቀናው በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያገኛል። የ48 ዓመቱ ዳንኤሌ ዴቬሪ ተጠባቂውን የደርቢ ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል።
የኤፍኤ ካፕ ጥሎ ማለፍ የሶስተኛ ቀን ውሎ
Mar 8, 2026 48
አዲስ አበባ ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፡- በእንግሊዝ ኤፍኤ ካፕ አምስተኛ ዙር መርሐ-ግብር የሶስተኛ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ፉልሃም ከሳውዝሃምፕተን በክራቨን ኮቴጅ ስታዲየም ይጫወታሉ። በአራተኛው ዙር ፉልሃም ስቶክ ሲቲን፣ ሳውዝሃምፕተን ሌይስተር ሲቲን አሸንፈዋል። ፉልሃም በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ፣ ሳውዝሃምፕተን በሻምፒዮንሺፕ (ሁለተኛ ዲቪዚዮን) የሚገኙ ክለቦች ናቸው። በሌላኛው መርሐ-ግብር ፖርት ቫሌ ከሰንደርላንድ ከቀኑ 10 ከሰዓት ከ30 ላይ በቫሌ ፓርክ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በእንግሊዝ ሶስተኛ የሊግ እርከን (ሊግ ዋን) የሚገኘው ፖርት ቫሌ በአራተኛው ዙር ብሪስቶል ሲቲን በማሸነፍ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅሏል። የፕሪሚየር ሊጉ ክለብ ሰንደርላንድ ኦክስፎርድ ዩናይትድን በመርታት 16 ውስጥ ገብቷል። ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ሊድስ ዩናይትድ ከኖርዊች ሲቲ ይጫወታሉ። በአራተኛው ዙር ሊድስ ዩናይትድ በርሚንግሃም ሲቲን፣ ኖርዊች ሲቲ ዌስትብሮሚች አልቢዮንን በማሸነፍ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅለዋል። አሸናፊ ቡድኖች ለሩብ ፍጻሜ ያልፋሉ። ሊቨርፑል፣ አርሰናል፣ ቼልሲ እና ማንችስተር ሲቲ እስከ አሁን ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀሉ ክለቦች ናቸው።
በሴቶች ድምፅና ተሳትፎ የኢትዮጵያ ብልፅግና እውን ይሆናል- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Mar 8, 2026 76
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ በሴቶች ድምፅና ተሳትፎ የኢትዮጵያን ብልፅግና እናረጋግጣለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። 50ኛው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በአዲስ አበባ ተካሄዷል። ስፖርታዊ መርሃ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሴቶች በሀገር ግንባታና በብልፅግና ጉዞ ውስጥ ያላቸውን የማይተካ ሚና አጽንኦት ሰጥተዋል። በኢትዮጵያ ታሪክ በርካታ ስኬተማ ሰዎችና ዝነኛ አትሌት ሴቶች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ ይህ የላቀ ብቃትና ጥንካሬ ትልቅ እውቅና ሊሰጠው እንደሚገባ ገልጸዋል። ሴቶች ለኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ትልቅ መስዋዕትነት መክፈላቸውን ያስታወሱት ከንቲባዋ፤ አሁንም ሴቶች ሀገራዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከወንድሞቻችን ጋር ተሳስረን ሀገራችንን እናሳድጋለን በማለት የሴቶች ተሳትፎ ከወንዶች ጋር በተቀናጀና በተደጋገፈ መልኩ ለሀገር ግንባታ እንደሚውል አመልክተዋል። ከንቲባዋ መንግሥት የሴቶችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። በብልፅግና ጉዞ ውስጥ የሴቶች የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ተጠቃሚነት በፍትሐዊነት እውን እንዲሆን በትጋት እንደሚሰራም ቃል ገብተዋል። ሴቶች የኢትዮጵያ የብልፅግና ጉዞ መሪ ኃይል መሆናቸውን የገለጹት ከንቲባዋ፤ ቀኑን ምክንያት በማድረግ እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ላለፉት 50 ዓመታት የሴቶች መብትና ድምፅ ትኩረት እንዲያገኝ በተደረገው ጥረት፣ ዛሬ ላይ ለደረሰው ትልቅ ሀገራዊ ለውጥ መሠረት መጣሉን ገልጸዋል። ሴቶች በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ዘርፎች እያመጡት ያለው ውጤት ለሀገሪቱ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን አውስተዋል። የሴቶች መብት እንዲከበርና የውሳኔ ሰጪነት ሚናቸው እንዲያድግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጠቆም፣ እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል። በውድድሩ የተሳተፉ ሴቶች ሩጫው የሴቶችን የአካልና የአዕምሮ ጤና ከመጠበቅ ባለፈ፣ ማህበራዊ ግንኙነትን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። በ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ሀላፊዎች ተዋቂ አትሌቶችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል
Mar 8, 2026 46
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሐ-ግብር በሲዳማ ቡና እና መቻል መካከል ዛሬ ይደረጋል። ጨዋታው ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይካሄዳል። ሲዳማ ቡና በሊጉ ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በስድስቱ ድል ሲቀናው በሰባቱ ተሸንፏል። በቀሪ ሶስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 16 ግቦችን ሲያስቆጥር 22 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ21 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቻል በበኩሉ በ16 ጨዋታዎች በዘጠኙ ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። 26 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 10 ጎሎች ተቆጥረውበታል። መቻል በ32 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በ16ኛ ሳምንት ሲዳማ ቡና አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። መቻል ከሸገር ከተማ ሁለት አቻ ተለያይቷል። ሲዳማ ቡና ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ መቻል ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። ሁለቱ ቡድኖች በመጀመሪያው ዙር በአራተኛ ሳምንት ባደረጉት ጨዋታ ሁለት አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው። በወቅቱ ቱሪስት ለማ ሁለቱን ግቦች ለመቻል አስቆጥራለች። ምትኬ ብርሃኑ የሲዳማ ቡናን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፋለች።
አካባቢ ጥበቃ
የአባያና ጫሞ ሀይቆችን ከስጋት መታደግ የሚያስችል የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ ይሰራል
Mar 7, 2026 114
አርባ ምንጭ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ የስምጥ ሸለቆ ተፋሰስ የሆኑ የአባያና ጫሞ ሀይቆችን ከስጋት ለመታደግ የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ እንደሚሰራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተባባሪነት የአባያና ጫሞ ሀይቆች የሚያስከትሉትን ተጽእኖ መቀነስ የሚያስችል የባለድርሻ አካላት ውይይት በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት የአባያና ጫሞ ሀይቆችን በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሉ ከፀጋነት ወደ ስጋትነት እየተቀየሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተለይ በጋሞ፣ በጋርዱላ፣ በኮንሶና በቡርጂ ዞኖች የሚገኙ አርሶ አደሮችን ማሳ እንዲሁም በተለያዩ መሠረተ ልማቶች ላይ አደጋ እያስከተሉ ይገኛሉ ብለዋል። በመሆኑም ሐይቆቹን ከስጋት ለመታደግ የተቀናጀና በጥናት የተደገፈ ስራ እንደሚጠናከር ገልጸዋል፡፡ ተፋሰሶቹ የተፈጥሮ ስነ-ምህዳር፣ የፍራፍሬ፣ የብዝሃ ህይወት የቱሪዝምና የቀጣናዊ ልማት ማሳለጫዎች መሆናቸውን ጠቅሰው ከስጋት ወደ ሀብት ምንጭነት ለመቀየር የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በውሃው ዘርፍ የረጅም ጊዜ ልምድ ያለው አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉን ችግሮች ለመቅረፍ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው የክልሉ መንግስት የበኩሉን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። የማዕድን ሚኒስትርና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በበኩላቸው የአባያና ጫሞ ሃይቆችን በዘላቂነት መጠቀም ለሃገር ሁለንተናዊ ብልጽግና ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በአርባ ምንጭና አካባቢው መልከ ብዙ ፀጋዎች መኖራቸውን ጠቅሰው የሀይቆቹን ትሩፋት ለማጉላት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በአግባቡ ሊከናወን እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተገኙ ጥናቶች መሠረት የተፋሰሶቹን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ፕሮግራሞች፣ ስትራቴጂዎችና ፕሮጀክቶች ተቀርጸው መተግበር እንዳለባቸውም አመልክተዋል። የአባያና ጫሞ ሀይቆች የውሃ መጠን መጨመር፣ የተፋሰሱ ወንዞች ሙላትና ደለል ከፍተኛ አካባቢያዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎችን እያስከተሉ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አብደላ ከማል(ዶ/ር) ናቸው። የአባያና ጫሞ እንዲሁም ሌሎች ተፋሰሶች በተቀናጀ ሁኔታ ካልተመሩ ተጽዕኖው ከሀይቆቹ ዳርቻ አልፎ ሰፊ ቦታዎችን ሊያዳርስ እንደሚችል በጥናት መረጋገጡንም ጠቅሰዋል። ዩኒቨርሲቲው በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ምክንያቶች የሚከሰቱ ተግዳሮቶችን በሳይንሳዊ መንገድ ለመከላከል የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የስራ ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎችም እየተሳተፉ ነው።
የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ተምሳሌታዊ ተግባር ነው
Mar 7, 2026 76
አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አርአያ የሚሆን ስራ እያከናወነች እንደምትገኝ የዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን ገለጹ። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባትና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን ማምረት፣ አረንጓዴ አሻራ፣ የስንዴ ምርታማነት፣ የኢትዮጵያ የማዳበሪያ እና የጤናማ አፈር ፍኖተ ካርታ፣ አነስተኛ ይዞታ ያላቸውን የመስኖ ስራዎች ማስፋትና የተራቆቱ መሬቶችን በአካባቢ ጥበቃ ስራ ወደ ነባር ይዞታቸው መመለስ ከተከናወኑ ተግባር መካከል ይጠቀሳሉ። የዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እየገነባች ያለችው አቅም የሚደነቅ መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ስኬታማ ስራዎችን እያከናወነች እንደሚገኝ ጠቅሰው እንደ አረንጓዴ አሻራ ባሉ ኢኒሼቲቮች የቀጣናው ሀገራት ተጠቃሚ ሊሆኑ እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የዘርፉ ስኬቶች ለማስፋት መንግስት፣ ቀጣናዊ ተቋማት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይበልጥ ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸውም አመልክተዋል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በቀጣናው የሚገኙ ሀገራት በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ያላቸውን አቅም የበለጠ ማጠናከር እንደሚኖርባቸውም ነው ባለሙያው የገለጹት። በዚህ ረገድ የዓለም ባንክ ከመንግስታት ጋር የግሉ ዘርፍ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ያለውን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለማሳደግና በተለይም ለወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኢኖቬሽን፣ ዲጂታል መፍትሄዎች፣ ዘላቂ የኢነርጂ አጠቃቀም እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑንም ነው ያነሱት። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የዓለም የግብርና ፋይናንስ ከፍተኛ ለውጥ ማሳየቱን ገልጸው ሀገራት ፋይናንስ በዘላቂነት የሚያመጡ አጋርነቶችን መፍጠር እንዳለባቸው መክረዋል። ለዚህ ተቋማት ትስስራቸውን ማጠናከር፣ አማራጭ ፋይናንስ መፈለግ፣ እሴት መጨመር ትኩረት መስጠት እና ለጋራ ግብ በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ ነው
Mar 6, 2026 192
ጋምቤላ ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች በቀጣዮቹ ሶስት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ መሆኑን በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋምቤላ ክልል ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አስታወቀ። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል በኢንስቲትዩቱ የጋምቤላ ክልል የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋሁን ዓለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ወይና ደጋማ አካባቢ በቀጣይ ወራት የሚኖረው የበልግ ዝናብ ለእርሻ ስራ ተስማሚ ነው። በክልሉ ወይና ደጋማ የአየር ፀባይ ያለው የማጃንግ ዞን በቀጣዩቹ ሶስት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለእርሻ ስራና ለእንስሳት ግጦሽ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር የአየር ትንበያ መረጃ ያመለክታል ብለዋል። በተለይም በዞኑ ቀድመው ለሚዘሩ የሰብል ዓይነቶችና ለመኸር እርሻ ስራ ዝግጅት በቂ የዝናብ ስርጭት እንደሚኖር መተንበዩን አመላክተዋል ። በሌላ በኩል ደግሞ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት በክልሉ ቆላማ አካባቢዎች ጠንከር ያለ የሙቀት መጠን እንደሚኖር የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጸዋል። በመሆኑም የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር የውሃ መጠን መቀነስ ሊኖር ስለሚችል ህብረተሰቡ ውሃን በአግባቡ መጠቀም እንዳለበት ምክር ሃሳብ ሰጥተዋል። እንዲሁም ከሙቀቱ መጨመር ጋር ተያይዞ በሰዎች ላይ የቆዳ ሽፍታ ሊከሰት ስለሚችል ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል
Mar 5, 2026 121
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አስከፊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም ገለጸ። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ተፈፃሚነት ያላት ቁርጠኝነት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንዳስቻላት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ተቋማዊ ልማት አማካሪ መንሱር ደሴ ገልጸዋል። ከየካቲት 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የአውደ ጥናት የምክክር መድረክ ተጠናቋል። በአውደ ጥናቱ ማጠናቀቂያ ላይ የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የአፍሪካ አስተባባሪ ጆንኪ ቴኑ፤ የአካባቢና የሥነ-ምኅዳር ደኅነንት ለማስጠበቅ ትብብርን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል። አውደ ጥናቱም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ተግባራዊ የተደረጉ መርሃ ግብሮችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ስኬታማ የልምድ ልውውጥና ግብዓት እንደተገኘበት ገልጸዋል። በፖሊሲዎችና የትኩረት መስኮች የተደረገው ውይይትም የዕውቀት ሽግግር የተደረገበት መሆኑን ተናግረዋል። ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የመንግሥታቱን ድርጅት የአየር ንብረት ስምምነት መነሻ በማድረግ ለተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ እያቀረበ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሀገራትም የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አስከፊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአካባቢ ጥበቃ ተቋም ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚያግዝ አረጋግጠዋል። በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ተቋማዊ ልማት አማካሪ መንሱር ደሴ በበኩላቸው፤ በአውደ ጥናቱ ከ14 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 150 ሙያተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ትግበራ ያላት ቁርጠኝነት በልማት አቅጣጫዎቿ ላይ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን አስረድተዋል። በአውደ ጥናቱም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም በተደረገ ድጋፍ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት መቅረባቸውን ተናግረዋል። ከሀምሌ ወር ጀምሮ ለአራት ዓመታት የሚተገበረው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም መርሃ ግብርም ከኢትዮጵያ የልማት አቅጣጫዎች ጋር ተጣጥመው እንደሚተገበሩ አንስተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በቀጣናው የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው -ኢጋድ
Mar 8, 2026 23
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂን ጨምሮ በቀጣናው የሴቶችን የአመራርና ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው። "መብቶች፣ ፍትህ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሴቶችን ቀን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፏል። ኢጋድ ለሴቶች አመራር ሰጪነት፣ አይበገሬነት እና በቀጣናው ሰላም፣ ብልጽግና እና ለውጥ ለማምጣት እያበረከቱት ላለው አስተዋጽኦ ክብር እና እውቅና እንደሚሰጥ ገልጿል። በኢጋድ ሴቶች በቀጣናው አመራር ሰጪነት ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። የኢጋድ የሰላም፣ ግብርና፣ ዲጂታል ደህንነት፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና መሬት አስተዳደር ፎረሞች እንዲሁም የኢጋድ የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂ ጨምሮ የተለያዩ ኢንሼቲቮች እየተገበረ መሆኑን አመልክቷል። የሴቶች ድምጽ እንዲሰማ እና መሉ ተሳትፏቸው እንዲረጋገጥ የሚያግዙ መድረኮችን መፍጠሩን ነው የኢጋድ ሴክሬተሪያት በመረጃው ያስታወቀው።
ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በሰላምና ደኅንነት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Mar 5, 2026 110
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢጋድ የሰላም እና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ውይይቱን ያደረጉት የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁን (ዶ/ር) በመወከል ነው። ውይይቱ ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም፣ ደኅንነት እና መረጋጋት ላይ ያላቸውን የጋራ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው። ሁለቱ ወገኖች የጋራ የተግባር ምላሽ ለመስጠት እና ስትራቴጂካዊ ትብብራቸውን ለማጎልበት ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የመንግሥታቱ ድርጅትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ ይገባል
Mar 4, 2026 207
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ እንደሚገባ ተገለጸ። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከጃፓን ኤምባሲ ጋር በመሆን የተባበሩት መንግሥታት ሪፎርም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል። የመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩ ቢሆኑም በተቋማዊ አወቃቀር ሥርዓት ላይ አፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ያገለሉ ናቸው። የአማኒ አፍሪካ ዳይሬክተር ሰለሞን አየለ ደርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት መዋቅር የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃ ሊወስድ ይገባል። በተቋማቱ የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥም ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ተከታታይ ሥራ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። የአህጉሪቱ አባል ሀገራትና ከሌሎች ሀገራት ጋር ትብብርን በማጠናከር የአፍሪካን የዓለምአቀፍ ተቋማት ፍትሐዊ ውክልና ማስከበር የሚስችል መዋቅራዊ የሪፎርም እርምጃ እንዲወሰድ መስራት ይገባል ብለዋል። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በአፍሪካ ሕብረትና የአፍሪካ ዳያስፖራ ጉዳዮች ላይ በጥናትና ምርምር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የጋና አምባሳደር ሮበርት አፍሪይ(ዶ/ር)፤ አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ተቋማት ያቀረበችው ፍትሐዊ የውክልና ጥያቄ ችላ በመባሉ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ የሌላት ብቸኛ አህጉር አድርጓታል ብለዋል። ለዚህም የመንግስታቱ ድርጅት አፍሪካ በተሸከመችው የጸጥታው ምክር ቤት የሥራ ጫና ልክ ውክልና የሚያስገኛትን የሪፎርም እምርጃ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። በአፍሪካ ሕብረት የጃፓን ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኖቦሩ ሴኪጉቺ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በመንግስታቱ የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ላይ ፍትሐዊ ውክልና ሊሰጣት ይገባል ብለዋል። ጃፓንም አፍሪካ በመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የሚኖራትን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። ጃፓንና የጂ-4 አባል ሀገራት የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡም አስታውቀዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2024 በጸደቀው "የወደፊት ስምምነት" ላይ የጸጥታው ምክር ቤት መዋቅራዊ የማሻሻያ እርምጃ ለመወሰድ የተቀመጠው አቅጣጫ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቀጣናዊ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Mar 1, 2026 172
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ እያሳደረ ባለው ከፍተኛ ተጽእኖ ምክንያት የቀጣናው የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እና የዜጎች የኑሮ መሰረት አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብ ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል።
ሐተታዎች
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 218
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 268
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 273
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 716
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 300
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 405
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1137
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1127
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3624
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2417
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8211
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6696
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 419
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 394
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።