ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ በዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች
Jan 10, 2026 31
አዲስ አበባ፤ ጥር 2 /2018 (ኢዜአ)፦ 46ኛው የዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ማምሻውን በአሜሪካ ፍሎሪዳ ተካሄዷል። ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በአምስት ርቀቶች በሁለቱም ጾታዎች በአጠቃላይ 20 አትሌቶችን አሳትፋለች። 10 ኪሎ ሜትር አዋቂ ወንዶች፣ 10 ኪሎ ሜትር አዋቂ ሴቶች፣ ከ20 ዓመት በታች ወንዶች 8 ኪሎ ሜትር፣ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች 6 ኪሎ ሜትር እና ድብልቅ ሪሌይ (4 በ 2 ኪሎ ሜትር) ኢትዮጵያ የተሳተፈችባቸው ርቀቶች ናቸው። የዛሬ ውድድሮችን ተከትሎ ኢትዮጵያ በሶስት የወርቅ፣ ሁለት የብር እና ሁለት የነሐስ በድምሩ ሰባት ሜዳሊያዎችን በማግኘት ኬንያን ተከትላ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ከ20 ዓመት በታች ሴቶች የስድስት ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት ማርታ ዓለማየሁ በ18 ደቂቃ 52 ሴኮንድ አንደኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ በሻምፒዮናው የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች። ኢትዮጵያ በአዋቂ የ10 ኪሎ ሜትር ወንዶች እና ሶሴቶች በቡድን ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችን አግኝታለች። በአዋቂ 10 ኪሎ ሜትር ወንድ ፍጻሜ አትሌት በሪሁ አረጋዊ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አግኝቷል። አትሌት ወሰኔ አሰፋ ከ20 በታች ሴቶች የስድስት ኪሎ ሜትር ውድድር ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች። በ10 ኪሎ ሜትር ሴቶች አትሌት ሰናይት ጌታቸው እና በድብልቅ ሪሌይ (ዱላ ቅብብል) የነሐስ ሜዳሊያዎች ተገኝተዋል። ኬንያ ሶስት የወርቅ፣ አራት የብር እና ሁለት የነሐስ በድምሩ ዘጠኝ ሜዳሊያዎችን በማግኘት አንደኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ዩጋንዳ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። አውስትራሊያ፣ ፈረንሳይ፣ ጃፓን እና አሜሪካ ሌሎች ሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ የገቡ ሀገራት ናቸው። ኢትዮጵያ በሻምፒዮና ተሳትፎ ታሪኳ የዘንድሮውን ጨምሮ 112 የወርቅ፣ 123 ብር እና 67 የነሐስ በድምሩ 302 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከኬንያ በመቀጠል ስኬታማዋ ሀገር ናት። ኬንያ የዘንድሮውን ጨምሮ ኬንያ 160 ወርቅ፣ 114 የብር እና 80 የነሐስ በድምሩ 354 ሜዳሊያዎችን በማግኘት የበላይነቱን ይዛለች።
ናይጄሪያ ለግማሽ ፍጻሜ አለፈች
Jan 10, 2026 52
አዲስ አበባ፤ ጥር 2 /2018 (ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሶስተኛ የሩብ ፍጻሜ መርሃ ግብር ናይጄሪያ አልጄሪያን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በማራካሽ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ቪክቶር ኦሲሜን በ47ኛው እና አኮር አዳምስ በ57ኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ኦሲሜን በውድድሩ ላይ ያስቆጠራቸውን ግቦች ብዛት ወደ አራት ከፍ በማድረግ በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክሩ አምስት ግቦች ያለውን የሞሮኮውን ብራሂም ዲያዝ ተከትሎ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በጨዋታው ላይ ናይጄሪያ በተጋጣሚዋ ላይ ከፍተኛ ብልጫ ወስዳለች። ንስሮቹ ተጨማሪ ግቦችን ለማስቆጠር የሚችሉባቸውን እድሎች አልተጠቀሙም። ውጤቱን ተከትሎ ናይጄሪያ ግማሽ ፍጻሜ የገባች ሶስተኛ ሀገር ሆናለች። በግማሽ ፍጻሜው ከአዘጋጇ ሞሮኮ ጋር የምታደርገው ጨዋታ ከወዲሁ ተጠባቂ ነው። ምሽት አራት ሰዓት ላይ የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቯር ከግብጽ በአጋዲር ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።
ማንችስተር ሲቲ ኤክስተር ሲቲን 10 ለ 1 በማሸነፍ በኤፍኤ ካፕ ቀጣዩን ዙር ተቀላቀለ
Jan 10, 2026 52
አዲስ አበባ፤ ጥር 2 /2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ኤፍኤካፕ የሶስተኛ ዙር መርሃ ግብር ማንችስተር ሲቲ ኤክስተር ሲቲን 10 ለ 1 ረቷል። ማምሻውን በኢትሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሮድሪ፣ ራያን ማይካዶ፣ ማክስ አሊይን፣ ሪኮ ሉዊስ፣ አንቶዋን ሴሜንዮ፣ ናታን አኬ፣ ቲጃኒ ራይንደርስ፣ ኒኮ ኦራይሊ እንዲሁም የኤክስተሮቹ ጃክ ፊትዝዋተር እና ጃክ ዶይል-ሄይስ በራሳቸው ላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጆርጅ ቢርች ለኤክስተር ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ከቦርንማውዝ የፈረመው አንቶዋን ሴሜኒዮ የመጀመሪያ ጎሉን ለሲቲ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ ወደ አራተኛ ዙር አልፏል።
ኢትዮጵያ መድን ወደ አሸናፊነት ተመልሷል
Jan 10, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 2 /2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 14ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮጵያ መድን ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በረከት ካሌብ እና ብሩክ ሙሉጌታ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ቴዎድሮስ ኃይለማርያም ለወላይታ ድቻን ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከአምስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ኢትዮጵያ መድን በ16 ነጥብ ደረጃውን ከ16ኛ ወደ 15ኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ አራተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በውድድር ዓመቱ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወላይታ ድቻ በ12 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ጨዋታውን ተከትሎ የ14ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የ5ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳሉ።
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዲጂታላይዝ የሆነ አሰራሩን ማጠናከር ይገባዋል
Jan 10, 2026 79
አዲስ አበባ፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የሪፎርም ስራዎችን በመተግበር አሰራሩን ዲጂታላይዝ በማድረግ የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስገነዘበ። የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ ምክትል ሰብሳቢዎች እና ከምክር ቤቱ ሴቶች ኮከስ አመራር አባላት ጋር ውይይት አካሂዷል። ውይይቱም የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን እያከናወናቸው በሚገኙ የሪፎርም እና የዲጂታል ስራዎች፣ የግዥና ንብረት የህግ ማዕቀፎች እንዲሁም ወደፊት በትኩረት ሊሰራባቸው በታቀዱ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ ፤ ባለስልጣኑ ሪፎርም ስራዎችን በመተግበር አሰራሩን ዲጂታላይዝ በማድረግ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ማጠናከር እንዳለበት ተናግረዋል። ባለስልጣኑ በተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ በመንግስት ግዥና ንብረት ዲጂታላይዜሽን፣ ከዘለቄታዊነት የግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓት በማጎልበት ከመንግስት ግዥና ንብረት አገልግሎት እና መረጃ ጥራትና ሽፋን ለማሳደግ ያከናወነው ስራ ለሌሎችም ተቋማት በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ገልጸዋል። ተቋሙ እየተገበረ በሚገኘው ዘመናዊ አሰራር ከሀገር አልፎ ለሌሎች ሀገራትም ልምድ እያካፈለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በመንግስት ግዥ ውጤታማ እንዲሆንና ግልጸኝነት ያለው አገልግሎት እንዲሳለጥ በማድረግ በኩል እያከናወነ ያለውን ተግባር ሊያጠናክር እንደሚገባ ገልጸዋል። የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ በበኩላቸው፤ ተቋሙ በዘመናዊ አሰራር በመታገዝ የግዥ ስርዓቱን ለማዘመንና የቁጥጥር ስርዓቱን ከማጠናከር አኳያ በርካታ ስራዎች እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ከግዥ ጋር ተያይዞ ያለውን ግልጸኝነት ከማረጋገጥ እና ህገ-ወጥነት ለመከላከል የሚያስችሉ የተለያዩ ዘመናዊ ስርዓቶችን መዘርጋቱን አብራርተዋል። ባለስልጣኑ የአሰራር ስርዓቱን ጥራትና ቅልጥፍና ለማሳደግ አዋጁን፣ መመሪያዎችንና የአሰራር ስርዓቶችን ተግባራዊ በማድረጉ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመዋል። ለተገልጋዮች እና ለባለድርሻ አካላት ተከታታይ ሥልጠና መስጠቱንም ገልጸዋል። በተለይ የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥን (e-GP) ከፌዴራል ተቋማት አልፎ ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የማውረድ ስራዎች ማከናወኑን ጠቁመዋል። በውይይት የተሳተፉና አስተያየታቸውን የሰጡት የተለያዩ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች በበኩላቸው፤ ተቋሙ አሰራሩን ዘመናዊ እና ግልጸኝነት በማስፈን እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ እንደገለጹት፤ ተቋሙ አሰራሩን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የሚያከናውናቸው ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው። የመንግስት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የመንግስት ግዥ ስርዓት ግልጽና ፍትሃዊ እንዲሆን እየተደረገ ያለው የመቆጣጠር ስራ የሚበረታታ መሆኑን ነው የገለጹት። ተቋሙ ከራሱ አልፎ ሌሎች ተቋማትን በዘመናዊ አሰራር ለማዘመን እያደረገ ያለው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን ጠቁመዋል። የመንግስት ልማት ድርጅት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ መለሰ መና በበኩላቸው፤ ባለስልጣኑ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ያደረገው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ገልጸዋል። የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እጸገነት መንግስቱ በበኩላቸው፤ ባለስልጣኑ በምክር ቤቱ የወጡ አዋጆችን በአግባቡ በመተግበር ለሌሎችም ተቋማት ምሳሌ መሆኑን ገልጸዋል። ባለስልጣኑ የጀመረውን ተግባር በማጠናከር ለወደፊት የላቁ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባው አሳስበዋል።
ፖለቲካ
ርዕይ አቅጣጫ ይሰጣል። መደመር ጥንካሬን ያጎናፅፋል። እነዚህ ተደምረው ነገን ይገነባሉ።
Jan 10, 2026 82
ርዕይ አቅጣጫ ይሰጣል። መደመር ጥንካሬን ያጎናፅፋል። እነዚህ ተደምረው ነገን ይገነባሉ። #PMOEthiopia የቢሾፍቱ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ይሆናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቢሾፍቱ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን በይፋ አስጀመሩ
በኢትዮጵያ በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች ለትውልድ ምንዳ ማውረስ የሚያስችሉ ናቸው -ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)
Jan 10, 2026 64
ባህር ዳር፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት አመታት በሁሉም ዘርፎች የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች ለትውልድ ምንዳ ማውረስ የሚያስችሉ ናቸው ሲሉ በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ተናገሩ። ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ አመራሮች በተገኙበት የ6 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ መድረክ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት አመታት በሁሉም ዘርፎች የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች ለትውልድ ምንዳ ማውረስ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። ለዚህም ብልጽግና ፓርቲ ትናንትን፣ ከዛሬና ነገ ጋር አሰናስሎና አስተሳስሮ ለትውልድ ምንዳ ለማውረስ የሚያስችሉ ስኬታማ ስራዎችን አከናውኗል ብለዋል። ፓርቲው በተለይም ባለፉት ዓመታት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የዲፕሎማሲ ድሎችን ማስመዝገቡን አንስተው ከተረጅነት የመውጣት ጥረትም ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በቴክኖሎጂ፣ በኢንዱስትሪ እና ሌሎችም ብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፎች የላቀ ስኬት ተመዝግቧል ብለዋል። በግንቦት ወር የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃ፣ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲከናወን ብልጽግና የድርሻውን ለመወጣት ከወዲሁ ዝግጅት ማድረጉንም ተናግረዋል። በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፤ በክልሉ ተከስቶ የነበረውን የፀጥታ ችግር በመቀልበስ ወደ ዘላቂ ሰላምና የተሟላ ልማት መገባት መቻሉን ገልጸዋል። በክልሉ በተለይም ለሰላም አማራጭ ትኩረት በመስጠት ስኬታማ ስራ መሰራቱን አንስተው የሰላምን አማራጭ በሚገፋ የጥፋት ቡድን ላይም የተጠናከረ ህግ የማስከበር እርምጃ መወሰዱን አንስተዋል። ለሁለት ቀናት የሚካሄደው መድረክ ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ተገምግሞ ቀጣይ አቅጣጫ ላይ ውይይት የሚደረግ መሆኑ ታውቋል።
የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሁሉም መስኮች የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘባቸው ነው
Jan 10, 2026 83
ሰመራ፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሁሉም መስኮች የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘባቸው መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ ተናገሩ። "ጠንካራ አደረጃጀት ለጠንካራ ፓርቲ" በሚል መሪ ሀሳብ በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 የ6 ወራት አፈፃፀም ግምገማ እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ መድረክ በሰመራ ከተማ እየተካሄደ ነው። መድረኩን ያስጀመሩት የብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ እንዳሉት ፓርቲው የኢትዮጵያን ብልፅግና የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። እየተከናወኑ በሚገኙ የልማት ስራዎችም የብልፅግና አይቀሬነት እየተረጋገጠ መምጣቱን ጠቅሰው ከዚህ ውስጥ አንዱ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መሆኑን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመትም ሀገርን ወደ ከፍታ ያሸጋገሩ ሌሎች ትላልቅ ፕሮጀክቶች የተፈጸሙበት እና ይፋ የተደረጉበት መሆኑንም ገልጸዋል። ለከተሞች ዕድገት ወሳኝ የሆኑ አንፀባራቂ ስራዎች በተለያዩ ከተሞች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው ይኼም ከተጠቃሚነት አኳያ የህብረተሰብን ጥያቄዎች መመለስ የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሁሉም መስኮች የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘባቸው መሆኑን ነው ያብራሩት። በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ መሐመድ ሁሴን በበኩላቸው ፓርቲው ባለፉት ዓመታት ሁሉንም አኩል ተሳታፊ እና ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በክልሉም ከዚህ በፊት ያልተለመዱ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው በሰመራ ከተማም የተከናወነው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋን ለነዋሪው ጽዱ እና ምቹ ማድረግ አስችሏል ብለዋል። በክልሉ በተለይም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚደረገው ጉዞ ተስፋ ሰጪ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወልኦ አይትሌ ናቸው።
አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት ነዋሪዎች መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Jan 9, 2026 338
ሮቤ ፤ጥር 1/2018 (ኢዜአ):-በኦሮሚያ ክልል ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በባሌ ዞን የሀረና ቡሉቅ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። የዞኑ አስተዳደር በበኩሉ በ189 ቀበሌዎች የተዋቀረው አደረጃጀት ለነዋሪዎች አገልግሎት በቅርበት ለመስጠት ከማስቻሉ ባለፈ ጊዜና ወጪን በመቆጠብ በልማት ሥራዎች ላይ እንዲያተኩሩ ማድረጉን ገልጿል። አዲሱን የቀበሌ አደረጃጀት በማስመልከት አስተያየታቸውን ከሰጡ የሀረና ቡሉቅ የቁምቢ ቀበሌ ነዋሪዎች መካከል አቶ ሀሰን አህመድ እንዳሉት፣ አደረጃጀቱ ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎቶች በቅርበት ለማግኘት አስችሏቸዋል። ከዚህ በፊት መንግስታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደ ወረዳና ከተማ አስተዳደር የሚያደርጉት ምልልስ ጊዜና ድካም እንደነበረው አስታውሰው "አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት ይህንን በማቃለል ተጠቃሚ አድርጎናል" ብለዋል። ሌላኛው ተገልጋይ አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው እንዳሉት የቀበሌ አደረጃጀቱ የህዝብን የልማት ተሳትፎ በማሳደግ ከዚህ በፊት የነበሩት የመሰረተ ልማት ችግሮች በህብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲፈቱ ዕድል ፈጥሯል። በአጭር ጊዜ ውስጥ ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከተከናወኑ የልማት ሥራዎች መካከል ድልድይና ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን ለአብነት ጠቅሰዋል። የሀረና ቡሉቅ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ሀሰን በበኩላቸው አዲሱ አደረጃጀት የወረዳውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በቅርበት ለመመለስ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። የባሌ ዞን አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ብርሃኑ አርፋሳ በበኩላቸው በዞኑ የሚገኙ 189 ቀበሌዎች በአዲሱ አደረጃጀት ተዋቅረው ወደ ሥራ መግባታቸውን ተናግሯል። በቀበሌ አደረጃጀቶችም አመራሮች ተመድበው ህብረተሰቡን በቅርበት እንዲያገለግሉ መደረጉን ገልጸዋል። እንደ አቶ ብርሀኑ ገለጻ በአዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት እየተሰጠ ያለው የህዝብ አገልግሎት ከዚህ በፊት ወደ ዞንና ወረዳዎች በተደጋጋሚ ይመጡ የነበሩ ቅሬታዎችን እየቀነሰና የህዝብ እርካታን እየጨመረ መጥቷል። በቀበሌዎቹ የተመደቡ አመራሮችና በለሙያዎች ህብረተሰቡን በተሻለ እንዲያገለግሉ የአቅም ግንባታ ሥልጠናና የድጋፍና ክትትል ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በቅርበት ለመፍታት አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት ተግባራዊ መደረጉ ይታወሳል። አደረጃጀቱ ህዝቡ በልማት ተጠቃሚ እንዲሆንና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎቹም በህዝብ ተሳትፎ መፍትሄ እንዲያገኙ ያለመ መሆኑ እንዲሁ።
ኢትዮጵያ እና ቻይና በዘርፈ-ብዙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ ለማጠናከር ተወያዩ
Jan 8, 2026 199
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ በርካታ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ አጠናክረው ማስቀጠል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ተቀብዬ በጽናት በሚጓዘው የኢትዮጵያ እና ቻይና የመንግሥት እና ሕዝብ ግንኙነት ላይ ተነጋግረናል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ ኢትዮጵያ እና ቻይና ለአስርት ዓመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። ይኽ ግንኙነት በቅርቡ ወደ በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የስትራቴጂክ ትብብር ማደጉንም አስታውቀዋል። በተለያዩ የልማት ትብብር ርዕሰ ጉዳዮችን ለማከናወን ያለንን ጽኑ አቋም በማስቀጠል ላይ ውይይት አድርገናልም ነው ያሉት። በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ
Jan 8, 2026 180
አዲስ አበባ ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ዛሬ መቀበላቸውንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። ጉብኝቱ የወል ፍላጎት በሆኑ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን ያካትታል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክቷል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
Jan 6, 2026 385
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም መሰረት፦ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የማዳበሪያ ምርት ፈቃድ እና የፖታሽ ማዕድን ምርት ፈቃድ ረቂቅ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ለምክር ቤቱ የቀረቡት ሁለት ረቂቅ ስምምነቶች የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር፣ ሀገራችን ለማዳበሪያ ግዥ የምታወጣውን ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ ለማስቀረት እና ለሀገራችን አርሶ አደሮች ወቅቱን የጠበቀ የማዳበሪያ ስርጭት እንዲኖር ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውና ከአካባቢ ጥበቃና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት አንጻርም የመንግስትን የፖሊሲ አቅጣጫ የተከተሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ የማዕድን ሚኒስቴር ስምምነቶቹን እንዲፈራረምና ወደ ስራ እንዲገቡ ምክርቤቱ በሙሉ ድምጽ ይሁንታ ሰጥቷል፡፡ 2. በመቀጠል የቤት ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ምከር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ ባለፉት አመታት በቂ የቤት አቅርቦት እንዲኖር የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም አሁንም የቤት አቅርቦትና ፍላጎት የተጣጣመ አይደለም፡፡ በመሆኑም በከተማና በገጠርለሚኖሩ ለሁሉም ዜጎች አቅምን ያገናዘበ፣ ተደራሽ እና በቂ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችል የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው ከኮሪያ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ ጋር በተደረገው የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት ላይ ነው፡፡ የብድር ስምምነቱ ለህከምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፕሮጄክት ምዕራፍ 2 ማስፈፀሚያ የሚውል 30,000,000 /ሰላሳ ሚሊዮን/የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኝ ሲሆን የሀከምና መሳሪያዎችን ችግር የሚፈታ፣ ዝቅተኛ ወለድ 0.01% የሚከፈልበት እና የከ5 አመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምከር ቤቱም ብድሩ ከሀገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋርየሚጣጣም መሆኑን በማረጋገጥ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው የተለያዩ አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ከፍያን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ተቋሙ ለተገልጋዮች ጥራትና ተዓማኒነት ያላቸው አገልግሎቶች ለመስጠት የሚያወጣቸውን ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ ወጪዎች የአገልግሎቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ ከሆነው የህብረተሰብ ክፍል ተመጣጣኝ ከፍያ በማስከፈል እንዲሸፍን ለማድረግ እንዲያስችለው ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምከር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይበሰፊው ከተወያየበት በኋላ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ደምጽ ወስኗል፡፡ 5. እንዲሁም የኅብረት ሥራ ማህበራት ማሻሻያ አዋጅ ምክር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 985/2009 ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ከተቀመጡ አቅጣጫዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማድረግ አዋጁን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 6. በማስከተልም የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቷል፡፡በአየር ትራንስፖርት ደህንነት፡ አስተማማኝነትና ቅልጥፍና ላይ የሚስተዋሉ የደህንነት ስጋቶችን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል አሰራር ለመተግበርየአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅ ቁጥር 432/1997ን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 7. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት ደንቦች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው የመሶብ አገልግሎትን ለማቋቋም የወጣው ደንብ ተገልጋዮች የመንግስት አገልግሎት ለማግኘት የሚያባከኑትን ጊዜ፣ ወጭ እና ጉልበት በመቆጠብ የተገልጋይ እርካታን የሚጨምርየአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ለመተግበር እንዲያስችል የቀረበ ሲሆን ሁለተኛው የኢትዮጵያ የብቃትና ሥራ አመራርኢንስቲትዩት አደረጃጀት፣ ሥልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣው ደንብ ተቋሙ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባርና ሃላፊነት ለመወጣት እንዲያስችለው ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ምክር ቤቱም በሁለቱም ደንቦች ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 8. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው የሁሉን አቀፍ የተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠን፣ ምንጭ እና አስተዳደርን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ደንቡ በኢትዮጵያ የኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 148/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ (3) መሰረት የተቋቋመው የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሁሉን አቀፍ ተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠንና ምንጭ እንዲሁም ፈንዱ ስለሚተዳደርበት ሁኔታ ለመወሰን ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 9. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲዊ ሪፐብሊክ የስፖርት ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የስፖርት ፖሊሲ የማህበረሰቡን የስፖርት ተሳትፎ ከማረጋገጥ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርአት ከመዘርጋት፣ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋት የአበረታች ቅመሞችና ዘዴዎች ከመከላከል እና ስፖርትን ለማህበራዊ ልማት ከመጠቀም አንጻር ከፍተቶች የነበሩበት በመሆኑ ፖሊሲውን ለማሻሻል ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 10. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የስፖርት ዘርፍ ካለው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲሁም አስተዳደራዊ ውስብስብነት አንጻር ዘርፉን በአግባቡ ለመምራት ዘመናዊ፣ አሳታፊና አካታች የሆነ የህግ ማዕቀፍና አስተዳደራዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
ፖለቲካ
ርዕይ አቅጣጫ ይሰጣል። መደመር ጥንካሬን ያጎናፅፋል። እነዚህ ተደምረው ነገን ይገነባሉ።
Jan 10, 2026 82
ርዕይ አቅጣጫ ይሰጣል። መደመር ጥንካሬን ያጎናፅፋል። እነዚህ ተደምረው ነገን ይገነባሉ። #PMOEthiopia የቢሾፍቱ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ይሆናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቢሾፍቱ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን በይፋ አስጀመሩ
በኢትዮጵያ በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች ለትውልድ ምንዳ ማውረስ የሚያስችሉ ናቸው -ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)
Jan 10, 2026 64
ባህር ዳር፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት አመታት በሁሉም ዘርፎች የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች ለትውልድ ምንዳ ማውረስ የሚያስችሉ ናቸው ሲሉ በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ተናገሩ። ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ አመራሮች በተገኙበት የ6 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ መድረክ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት አመታት በሁሉም ዘርፎች የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች ለትውልድ ምንዳ ማውረስ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። ለዚህም ብልጽግና ፓርቲ ትናንትን፣ ከዛሬና ነገ ጋር አሰናስሎና አስተሳስሮ ለትውልድ ምንዳ ለማውረስ የሚያስችሉ ስኬታማ ስራዎችን አከናውኗል ብለዋል። ፓርቲው በተለይም ባለፉት ዓመታት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የዲፕሎማሲ ድሎችን ማስመዝገቡን አንስተው ከተረጅነት የመውጣት ጥረትም ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በቴክኖሎጂ፣ በኢንዱስትሪ እና ሌሎችም ብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፎች የላቀ ስኬት ተመዝግቧል ብለዋል። በግንቦት ወር የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃ፣ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲከናወን ብልጽግና የድርሻውን ለመወጣት ከወዲሁ ዝግጅት ማድረጉንም ተናግረዋል። በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፤ በክልሉ ተከስቶ የነበረውን የፀጥታ ችግር በመቀልበስ ወደ ዘላቂ ሰላምና የተሟላ ልማት መገባት መቻሉን ገልጸዋል። በክልሉ በተለይም ለሰላም አማራጭ ትኩረት በመስጠት ስኬታማ ስራ መሰራቱን አንስተው የሰላምን አማራጭ በሚገፋ የጥፋት ቡድን ላይም የተጠናከረ ህግ የማስከበር እርምጃ መወሰዱን አንስተዋል። ለሁለት ቀናት የሚካሄደው መድረክ ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ተገምግሞ ቀጣይ አቅጣጫ ላይ ውይይት የሚደረግ መሆኑ ታውቋል።
የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሁሉም መስኮች የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘባቸው ነው
Jan 10, 2026 83
ሰመራ፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሁሉም መስኮች የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘባቸው መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ ተናገሩ። "ጠንካራ አደረጃጀት ለጠንካራ ፓርቲ" በሚል መሪ ሀሳብ በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 የ6 ወራት አፈፃፀም ግምገማ እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ መድረክ በሰመራ ከተማ እየተካሄደ ነው። መድረኩን ያስጀመሩት የብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ እንዳሉት ፓርቲው የኢትዮጵያን ብልፅግና የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። እየተከናወኑ በሚገኙ የልማት ስራዎችም የብልፅግና አይቀሬነት እየተረጋገጠ መምጣቱን ጠቅሰው ከዚህ ውስጥ አንዱ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መሆኑን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመትም ሀገርን ወደ ከፍታ ያሸጋገሩ ሌሎች ትላልቅ ፕሮጀክቶች የተፈጸሙበት እና ይፋ የተደረጉበት መሆኑንም ገልጸዋል። ለከተሞች ዕድገት ወሳኝ የሆኑ አንፀባራቂ ስራዎች በተለያዩ ከተሞች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው ይኼም ከተጠቃሚነት አኳያ የህብረተሰብን ጥያቄዎች መመለስ የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሁሉም መስኮች የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተገኘባቸው መሆኑን ነው ያብራሩት። በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ መሐመድ ሁሴን በበኩላቸው ፓርቲው ባለፉት ዓመታት ሁሉንም አኩል ተሳታፊ እና ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በክልሉም ከዚህ በፊት ያልተለመዱ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው በሰመራ ከተማም የተከናወነው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋን ለነዋሪው ጽዱ እና ምቹ ማድረግ አስችሏል ብለዋል። በክልሉ በተለይም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚደረገው ጉዞ ተስፋ ሰጪ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወልኦ አይትሌ ናቸው።
አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት ነዋሪዎች መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Jan 9, 2026 338
ሮቤ ፤ጥር 1/2018 (ኢዜአ):-በኦሮሚያ ክልል ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በባሌ ዞን የሀረና ቡሉቅ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። የዞኑ አስተዳደር በበኩሉ በ189 ቀበሌዎች የተዋቀረው አደረጃጀት ለነዋሪዎች አገልግሎት በቅርበት ለመስጠት ከማስቻሉ ባለፈ ጊዜና ወጪን በመቆጠብ በልማት ሥራዎች ላይ እንዲያተኩሩ ማድረጉን ገልጿል። አዲሱን የቀበሌ አደረጃጀት በማስመልከት አስተያየታቸውን ከሰጡ የሀረና ቡሉቅ የቁምቢ ቀበሌ ነዋሪዎች መካከል አቶ ሀሰን አህመድ እንዳሉት፣ አደረጃጀቱ ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎቶች በቅርበት ለማግኘት አስችሏቸዋል። ከዚህ በፊት መንግስታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደ ወረዳና ከተማ አስተዳደር የሚያደርጉት ምልልስ ጊዜና ድካም እንደነበረው አስታውሰው "አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት ይህንን በማቃለል ተጠቃሚ አድርጎናል" ብለዋል። ሌላኛው ተገልጋይ አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው እንዳሉት የቀበሌ አደረጃጀቱ የህዝብን የልማት ተሳትፎ በማሳደግ ከዚህ በፊት የነበሩት የመሰረተ ልማት ችግሮች በህብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲፈቱ ዕድል ፈጥሯል። በአጭር ጊዜ ውስጥ ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከተከናወኑ የልማት ሥራዎች መካከል ድልድይና ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን ለአብነት ጠቅሰዋል። የሀረና ቡሉቅ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ሀሰን በበኩላቸው አዲሱ አደረጃጀት የወረዳውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በቅርበት ለመመለስ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። የባሌ ዞን አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ብርሃኑ አርፋሳ በበኩላቸው በዞኑ የሚገኙ 189 ቀበሌዎች በአዲሱ አደረጃጀት ተዋቅረው ወደ ሥራ መግባታቸውን ተናግሯል። በቀበሌ አደረጃጀቶችም አመራሮች ተመድበው ህብረተሰቡን በቅርበት እንዲያገለግሉ መደረጉን ገልጸዋል። እንደ አቶ ብርሀኑ ገለጻ በአዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት እየተሰጠ ያለው የህዝብ አገልግሎት ከዚህ በፊት ወደ ዞንና ወረዳዎች በተደጋጋሚ ይመጡ የነበሩ ቅሬታዎችን እየቀነሰና የህዝብ እርካታን እየጨመረ መጥቷል። በቀበሌዎቹ የተመደቡ አመራሮችና በለሙያዎች ህብረተሰቡን በተሻለ እንዲያገለግሉ የአቅም ግንባታ ሥልጠናና የድጋፍና ክትትል ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በቅርበት ለመፍታት አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት ተግባራዊ መደረጉ ይታወሳል። አደረጃጀቱ ህዝቡ በልማት ተጠቃሚ እንዲሆንና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎቹም በህዝብ ተሳትፎ መፍትሄ እንዲያገኙ ያለመ መሆኑ እንዲሁ።
ኢትዮጵያ እና ቻይና በዘርፈ-ብዙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ ለማጠናከር ተወያዩ
Jan 8, 2026 199
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ በርካታ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ አጠናክረው ማስቀጠል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ተቀብዬ በጽናት በሚጓዘው የኢትዮጵያ እና ቻይና የመንግሥት እና ሕዝብ ግንኙነት ላይ ተነጋግረናል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ ኢትዮጵያ እና ቻይና ለአስርት ዓመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። ይኽ ግንኙነት በቅርቡ ወደ በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የስትራቴጂክ ትብብር ማደጉንም አስታውቀዋል። በተለያዩ የልማት ትብብር ርዕሰ ጉዳዮችን ለማከናወን ያለንን ጽኑ አቋም በማስቀጠል ላይ ውይይት አድርገናልም ነው ያሉት። በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ
Jan 8, 2026 180
አዲስ አበባ ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ዛሬ መቀበላቸውንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። ጉብኝቱ የወል ፍላጎት በሆኑ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን ያካትታል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክቷል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
Jan 6, 2026 385
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም መሰረት፦ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የማዳበሪያ ምርት ፈቃድ እና የፖታሽ ማዕድን ምርት ፈቃድ ረቂቅ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ለምክር ቤቱ የቀረቡት ሁለት ረቂቅ ስምምነቶች የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር፣ ሀገራችን ለማዳበሪያ ግዥ የምታወጣውን ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ ለማስቀረት እና ለሀገራችን አርሶ አደሮች ወቅቱን የጠበቀ የማዳበሪያ ስርጭት እንዲኖር ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውና ከአካባቢ ጥበቃና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት አንጻርም የመንግስትን የፖሊሲ አቅጣጫ የተከተሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ የማዕድን ሚኒስቴር ስምምነቶቹን እንዲፈራረምና ወደ ስራ እንዲገቡ ምክርቤቱ በሙሉ ድምጽ ይሁንታ ሰጥቷል፡፡ 2. በመቀጠል የቤት ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ምከር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ ባለፉት አመታት በቂ የቤት አቅርቦት እንዲኖር የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም አሁንም የቤት አቅርቦትና ፍላጎት የተጣጣመ አይደለም፡፡ በመሆኑም በከተማና በገጠርለሚኖሩ ለሁሉም ዜጎች አቅምን ያገናዘበ፣ ተደራሽ እና በቂ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችል የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው ከኮሪያ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ ጋር በተደረገው የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት ላይ ነው፡፡ የብድር ስምምነቱ ለህከምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፕሮጄክት ምዕራፍ 2 ማስፈፀሚያ የሚውል 30,000,000 /ሰላሳ ሚሊዮን/የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኝ ሲሆን የሀከምና መሳሪያዎችን ችግር የሚፈታ፣ ዝቅተኛ ወለድ 0.01% የሚከፈልበት እና የከ5 አመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምከር ቤቱም ብድሩ ከሀገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋርየሚጣጣም መሆኑን በማረጋገጥ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው የተለያዩ አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ከፍያን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ተቋሙ ለተገልጋዮች ጥራትና ተዓማኒነት ያላቸው አገልግሎቶች ለመስጠት የሚያወጣቸውን ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ ወጪዎች የአገልግሎቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ ከሆነው የህብረተሰብ ክፍል ተመጣጣኝ ከፍያ በማስከፈል እንዲሸፍን ለማድረግ እንዲያስችለው ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምከር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይበሰፊው ከተወያየበት በኋላ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ደምጽ ወስኗል፡፡ 5. እንዲሁም የኅብረት ሥራ ማህበራት ማሻሻያ አዋጅ ምክር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 985/2009 ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ከተቀመጡ አቅጣጫዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማድረግ አዋጁን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 6. በማስከተልም የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቷል፡፡በአየር ትራንስፖርት ደህንነት፡ አስተማማኝነትና ቅልጥፍና ላይ የሚስተዋሉ የደህንነት ስጋቶችን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል አሰራር ለመተግበርየአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅ ቁጥር 432/1997ን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 7. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት ደንቦች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው የመሶብ አገልግሎትን ለማቋቋም የወጣው ደንብ ተገልጋዮች የመንግስት አገልግሎት ለማግኘት የሚያባከኑትን ጊዜ፣ ወጭ እና ጉልበት በመቆጠብ የተገልጋይ እርካታን የሚጨምርየአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ለመተግበር እንዲያስችል የቀረበ ሲሆን ሁለተኛው የኢትዮጵያ የብቃትና ሥራ አመራርኢንስቲትዩት አደረጃጀት፣ ሥልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣው ደንብ ተቋሙ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባርና ሃላፊነት ለመወጣት እንዲያስችለው ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ምክር ቤቱም በሁለቱም ደንቦች ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 8. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው የሁሉን አቀፍ የተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠን፣ ምንጭ እና አስተዳደርን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ደንቡ በኢትዮጵያ የኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 148/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ (3) መሰረት የተቋቋመው የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሁሉን አቀፍ ተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠንና ምንጭ እንዲሁም ፈንዱ ስለሚተዳደርበት ሁኔታ ለመወሰን ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 9. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲዊ ሪፐብሊክ የስፖርት ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የስፖርት ፖሊሲ የማህበረሰቡን የስፖርት ተሳትፎ ከማረጋገጥ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርአት ከመዘርጋት፣ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋት የአበረታች ቅመሞችና ዘዴዎች ከመከላከል እና ስፖርትን ለማህበራዊ ልማት ከመጠቀም አንጻር ከፍተቶች የነበሩበት በመሆኑ ፖሊሲውን ለማሻሻል ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 10. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የስፖርት ዘርፍ ካለው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲሁም አስተዳደራዊ ውስብስብነት አንጻር ዘርፉን በአግባቡ ለመምራት ዘመናዊ፣ አሳታፊና አካታች የሆነ የህግ ማዕቀፍና አስተዳደራዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
ማህበራዊ
የሀላባ የዘመን መለወጫን በዓለም አቀፍ ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥናታዊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው
Jan 10, 2026 51
ቁሊቶ፤ ጥር 2/2018 (ኢዜአ)፡- የሀላባ የዘመን መለወጫ (ሴራ) በዓልን በዓለም አቀፍ ቅርስነት እንዲመዘገብ የሚያግዙ ጥናታዊ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን አስታወቀ። “ሴራ ባህላችን በኅብር የመቻል ዐቅም ማሳያች ነው” በሚል መሪ ሐሳብ በቁሊቶ ከተማ የሀላባ ባህል፣ ቋንቋና ታሪክ ሲምፖዚዬም ተካሂዷል፡፡ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር በዚሁ ወቅት፤ የሀላባ ሴራ በዓል ከዘመን መለወጫ በዓልነት ባለፈ ማኅበረሰባዊ ትሥሥርን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ባለሥልጣኑ ሀገር በቀል ዕውቀቶች እንዲጠበቁና ለትውልድ እንዲተላለፉ በጥናት የተደገፈ ሠነድ አዘጋጅቷል ብለዋል። የሀላባ የዘመን መለወጫ በዓል በዓለም አቀፍ ቅርስነት እንዲመዘገብ የሚያግዙ ጥናታዊ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አረጋግጠዋል። የሀላባ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ሙህዲን ሁሴን በበኩላቸው፤ የሴራ በዓል ባህላዊ ይዘቱን ጠብቆ ለተተኪው ትውልድ እንዲተላለፍ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል። የሀላባ የዘመን መለወጫ በዓል የመጠያየቅና የመተጋገዝ ዕሴት የሚጠናከርበት መሆኑን የገለጹት የውይይቱ ተሳታፊዎች፤ ይህን ለማስቀጠል መድረኩ ከፍተኛ ሚና ያበረክታል ብለዋል።
ኢትዮጵያን የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራት ይጠናከራሉ
Jan 10, 2026 92
አዲስ አበባ፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ በዲጂታል የታገዘ ደህንነቱና ፈዋሽነቱ የተረጋገጠ የምግብ፣ መድሀኒትና የጤና አገልግሎት መስጠት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። በኢትዮጵያ የጤና ቁጥጥር ስርዓትን ማጠናከር የሚያስችል የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ "ጠንካራ የጤና ቁጥጥር ለማይበገር የጤና ሥርዓት" በሚል መሪ ሀሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ተካሂዷል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች እንደ ሀገር ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ መከላከልን መሰረት ባደረገ የጤና ፖሊሲ የዜጎችን ጤናና ደህንነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶችን ማስመዝገቧን ገልጸዋል፡፡ ይህ የጤና ፖሊሲ መከላከልን መሰረት ከማድረግ ባለፈ ጥራቱና ደህንነቱ የተጠበቀ የህክምና አገልግሎት መስጠት እንዲያስችል ተደርጎ ተሻሽሏል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የጀመረችውን ጥረት ማሳካት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ ጠንካራ የጤና ቁጥጥር ሥርዓት በመዘርጋት ደህንነቱና ፈዋሽነቱ የተረጋገጠ የምግብ፣ የመድሀኒትና የጤና አገልግሎት ተደራሽ እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የተደረጉ የፖሊሲና የአሰራር ማሻሻያዎች የጤና ቁጥጥር ሂደቱን በማዘመን የማይበገር የጤና ሥርዓት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ከሶስት ዓመት በፊት የሀገር አቀፍ የመድሀኒት አቅርቦት በሀገር ውስጥ ምርት የሚሸፈነው ስምንት በመቶ ብቻ እንደነበር በማንሳት፤ በአሁኑ ወቀት 60 በመቶ ደርሷል ብለዋል፡፡ የጥራት መንደር ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች ዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችን ማቅረብ የሚያስችል ተቋም ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ ለሜዲካል ቱሪዝም መሰረት እንደሚጥልም ገልጸዋል፡፡ የሀገር ውስጥ የመድሀኒትና የህክምና መሳሪያዎች አቅርቦት መሻሻል ፈዋሽነቱና ደህንነቱ የተረጋገጠ ህክምና ከመስጠት ባለፈ ለሜዲካል ቱሪዝም የጎላ አበርክቶ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ አፍሪካውያን ለውጭ ህክምና አገልግሎት በዓመት እስከ አንድ ቢሊዬን ዶላር እንደሚያወጡ በመጥቀስ፤ ኢትዮጵያ ባለችበት ጂኦ ስትራቴጂ የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል መሆን እንደምትችል ገልጸዋል፡፡ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት የኢትዮጵያን አየር መንገድ እንደሚጠቀሙ በማንሳት፤ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የህክምና አገልግሎት በመስጠት የሜዲካል ቱሪዝምን የሚያረጋግጡ ተግባራት ይጠናከራሉ ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያን የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር ማሳደግና ዲጂታል ስርዓትን ማዘመን እንደሚገባም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ባለፉት አራት ዓመታት 260 ሺህ የጤና ባለሙያዎች በተለያዩ ዘርፎች በብቃት ሰልጥነው መመረቃቸውን ገልጸው፣ ይህም የጤና ቁጥጥር ስርዓቱን ለማጠናከር ገንቢ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ በጤናው ዘርፍ ያለውን ቁጥጥር በማጠናከር የማይበገር የጤና ስርዓት ለመገንባት የዲጂታል ስርዓት ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የኮሪደር ልማት ሥራዎች ለነዋሪዎች ምቹ ሁኔታ ፈጥረዋል
Jan 10, 2026 82
ይርጋጨፌ፤ ጥር 2/2018 (ኢዜአ)፡- የኮሪደር ልማት ሥራዎች የከተሞችን ገጽታ በመቀየር ለነዋሪዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን የጌዴኦ ዞን አሥተዳደር ገለጸ። በይርጋጨፌ ከተማ ሁለተኛው ዙር የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራ ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። የጌዴኦ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በዞኑ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች የከተሞችን ገጽታ በመቀየር እድገታቸውን እያፋጠኑና ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ እያደረጉ ነው። በዞኑ ዲላ፣ ይርጋጨፌና ወናጎን ጨምሮ በአምስት ከተሞች የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተሞችን ደረጃ በማሻሻል ተወዳዳሪነታቸውን አሳድጓል ብለዋል። በተለይም በጽዱ አካባቢ የመኖር ባህልን በማጎልበት ሕብረተሰቡ ለልማቱ ቅድሚያ እንዲሰጥ ማድረጉን አስገንዝበዋል። ዛሬ በይርጋጨፌ የተጀመረው የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራም የከተማዋን ውበትና ጽዳት በእጅጉ የሚያሳድግ መሆኑን አንስተዋል። የወንዝ ዳርቻ ልማቱ የውኃ ብክለትን በመቀነስ ጤናው በተጠበቀ አካባቢ የመኖር ባህልን የሚያጠናክር መሆኑን ጠቅሰው፤ ለልማቱ ስኬት ባለድርሻ አካላት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። የሕብረተሰብ ተሳትፎ በተለይም የግል ባለሃብቶች ተሳትፎን በማጠናከር የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ርብርብ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የኮሪደር ልማት ከተማዋን ምቹ ማድረጉን ያነሱት የይርጋጨፌ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ብዙአየሁ ታደሠ በበኩላቸው፤ ከተማዋን አቋርጠው የሚያልፉ ሦስት ወንዞች በአግባቡ ባለመያዛቸው ለብክለት መጋለጣቸውን ተናግረዋል። በፌጤ ወንዝ ላይ ዛሬ የተጀመረው ሁለተኛው ዙር የወንዝ ዳርቻ ልማት 750 ሜትር የእግረኛና የሳይክል መንገድ፣ የአረንጓዴ ስፍራና መዝናኛ ቦታዎችን ጨምሮ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች ማካተቱንም ጠቅሰዋል። ይህም የወንዙን ብክለት በማስቀረት ለከተማው ተጨማሪ ውበትና እድገት የሚያጎናጸፍ መሆኑን ነው ያስረዱት። ሥራውን በቀጣይ ሥድስት ወራት አጠናቅቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ጥረት እንደሚደረግም ነው ያመላከቱት። ሕብረተሰቡ ይዞታውን በማንሳት አጋርነቱን ማሳየቱን አንስተው፤ በልማቱም ተሳትፎውን ማጠናከር እንደሚጠበቅበት አስረድተዋል። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል መላከሰላም ድረስ ታደሠ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ ለወንዝ ዳርቻ ልማት ንብረታቸውን ማንሳታቸውን ተናግረው ልማቱ ፈጥኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። የፌጤ ወንዝ በተለያዩ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻዎች የተበከለ በመሆኑ ለጤና እክል ሲጋለጡ መቆየታቸውን ያነሱት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ ታምራት ታደሠ ናቸው። ዛሬ የወንዝ ዳርቻ ልማት ወደ ሥራ መግባቱ ብክለትን በማስቀረት ጽዱ አካባቢን ይፈጥራል ብለዋል።
የህግ ትምህርት ቤቱ የዘርፉን የሰለጠነ የሰው ሃይል ለማሳደግ እያገዘ ነው
Jan 10, 2026 83
አዲስ አበባ፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦የአዲሰ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት በዘርፉ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት እያገዘ መሆኑን የፍትሕ ሚኒስትር ሀና አርአያ ስላሴ ገለጹ። ዛሬ በዩኒቨርሲቲው የሕግ ትምህርት ቤቱ 62ኛ አመት የምስረታ በዓል ተከብሯል። ሚኒስትሯ በዚህ ወቅት እንዳሉት የሕግ ትምህርት ቤቱ በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ አስፈላጊ እውቀት እና ክህሎት የጨበጡ ተዋናዮችን በማፍራት ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዝ ነው። ዩኒቨርሲቲው ከስድስት አስርት ዓመታት በበለጠ ጉዞው ዳኞች፣ አቃብያነ ህጎችና ጠበቆችን ጨምሮ በዘርፉ ተሳታፊ የሆኑ በርካታ የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰዋል። ዩኒቨርስቲውና ምሁራኑ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት በመስራት የፖሊሲና የሕግ ማሻሻያ ስራዎችን ጨምሮ የሕግ ማርቀቅ ተግባራት ላይም የላቀ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ነው የገለጹት። በተለይም የህግ ትምህርት ቤቱ ምሁራን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በቅንጅት መስራታቸው ጥራት ያላቸው ህጎች እንዲወጡና ተግባራዊ እንዲደረጉ እያገዘ መሆኑንም ነው የገለጹት። በተጨማሪም በተቋሙ የሚሰሩ የዘርፉ ምሩቃን በትምህርት ቤት ያገኙትን እውቀትና ክህሎት በተጨባጭ በስራ ላይ እንዲያውሉ ለማድረግም በትብብር መስራቱ ሰፊ እገዛ ያለው መሆኑን ነው ያነሱት። እንደ ሀገር የሕግ ትምህርት እና የሕግ ምርምር ላይ በቅንጅት መስራት የፍትሕ ስርዓቱን ጠንካራ ለማድረግ ትልቅ አበርክቶ እንዳለው ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በሀገሪቱ የፍትሕ ስርዓት እንዲቀረጽና እንዲተገበር በማድረግ ሰፊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ነው የተናገሩት። በተለይም የሕግ ትምህርትን ለማስፋፋትና በመላው ሃገሪቱ በፍትሕ ስርዓቱ ውስጥ ተቋማት የሚሰጡት አገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል ከማድረግ አንፃር ስኬታማ ስራዎችን መስራቱንም አመልክተዋል። ባለፉት 62 ዓመታት ውስጥም 57 ዙር ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን ባለሙያዎቹ ከሀገር ውስጥ ባለፈም በውጭ ሀገራት በዘርፉ የተሻለ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል። በዩኒቨርሲቲው የህግ ትምህርት ቤት ዲን ፕሮፌሰር ሙራዱ አብዶ፤ የሕግ ትምህርት ቤቱ በዘርፉ የሰው ሀይል ከማፍራት በተጨማሪም ለማሕበረሰቡ ነፃ የህግ አገልግሎት በመስጠት ማሕበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በፍትሕ ስርዓቱ ዋና ተዋናይ የሆኑ ጠበቆች፣ዳኞች፣ተመራማሪዎችንና አማካሪዎችን በማፍራት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የፍትሕ ሚኒስትሯ ሀና አርአያ ስላሴን ጨምሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እንዲሁም የቀድሞ ተማሪዎች ተገኝተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ኢኮኖሚ
የባህር ዳር ከተማን የቱሪዝም መዳረሻነት የበለጠ ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ናቸው
Jan 10, 2026 57
ባህርዳር ፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦ የባህር ዳር ከተማን የቱሪዝም መዳረሻነት የበለጠ ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን በብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር) ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ አመራሮች በባህር ዳር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ዛሬ ማምሻውን ጎብኝተዋል። የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊው ሰማ ጥሩነህ (ዶር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ የባህር ዳር ከተማን ይበልጥ በማዘመን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ናቸው። የከተማ አስተዳደሩ ነዋሪውን በማስተባበር በኮሪደር ልማት፣ በስታዲየም ግንባታ፣ የአስፋልት መንገድ ግንባታ፣ በአረንጓዴ ስፍራዎችና ሌሎች የልማት ስራዎች ያከናወነው የልማት ስራ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ይህም ከተማዋን ከሀገር አቀፍና ከሌሎች የአለም ከተሞች ጋር በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስህቧ ተወዳዳሪ እንድትሆን ማድረጉን በምልከታቸው ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል። የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት፤ ከተማዋን የበለጠ የቱሪዝምና ኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ በርካታ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው። በከተማዋ እየተገነባ ያለው የኮሪደር ልማት ለኑሮ፣ ለመዝናኛና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ አድርጓታል ብለዋል። ስማርት ባህርዳርን በመተግበር፣ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን እውን በማድረግ ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። አመራሮቹ የኮሪደር ልማት፣ አዲሱን የአባይ ድልድይ እንዲሁም በጣናነሽ ቁጥር 2 ጀልባ በጣና ሃይቅ ላይ ሽርሽር በማድረግ ሌሎች የመሰረተ ልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የአፍሪካ አቪዬሽን ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው
Jan 10, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የአፍሪካን አቪዬሽን እድገት አስሮ የያዘውን የመሰረተ ልማት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታው በሁለት ምዕራፎች ተከፍሎ የሚከናወን ነው። የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ስርዓት የዘመናት ስብራት ምላሽ የሚሰጥ ነው በመጀመሪያው ምዕራፍ የሚገነባው አውሮፕላን ማረፊያ በዓመት 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል ብለዋል። በዚህ ምዕራፍ አንድ እጅግ ትልቅና ዘመናዊ እንዲሁም አንድ መለስተኛ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናሎች እንደሚገነቡ ጠቅሰዋል። ሁለት በተጓዳኝ የሚሰሩ የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች እንዲሁም 180 አውሮፕላኖችን በአንድ ጊዜ ማቆም የሚያስችል ቦታ ይገነባልም ብለዋል። በተጨማሪ 350 ማረፊያ ክፍሎች ያሉት ዘመናዊ ሆቴል በተርሚናሉ ውስጥ እንደሚገነባም ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የተናገሩት። በዓመት አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ቶን ጭነት የሚያስተናግድ የካርጎ ተርሚናል እና የአውሮፕላን ጥገና ማዕከልም በዚሁ ምዕራፍ እንደሚገነባ አስታውቀዋል። አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ ከነባሩ የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር በፈጣን ባቡር እና በፈጣን የመኪና መንገድ እንደሚገናኝ አስረድተዋል። ይህ ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የአፍሪካን አቪዬሽን እድገት አስሮ የያዘውን የመሰረተ ልማት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ፕሮጀክቱ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ አህጉርም ትልቅ አርአያ እንደሚሆን ተናግረዋል።። በተለይም የአፍሪካ ነፃ አህጉራዊ ንግድ ቀጣናን ተግባራዊነት ለማቀላጠፍና የአህጉሪቱን የንግድና የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር ቁልፍ ሚና ይጫወታል ብለዋል። አውሮፕላን ማረፊያው ከፍተኛ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ ከአውሮፕላን ማረፊያው ጋር ተያይዞ የሚመሰረተው የኤርፖርት ከተማም በንግድ፣ በኢንዱስትሪና በቱሪዝም ዘርፎች ለአካባቢው ዕድገት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አብራርተዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመሠረተ ልማትና ፕላኒንግ ክፍል ኃላፊ አቶ አብረሃም ተስፋዬ በበኩላቸው፤ አካባቢው አሁን ለሚሰራውም ሆነ ለወደፊት ተያያዥ የማስፋፊያ ስራዎች አመቺ እንደሆነ ገልፀው፤ ቦታው ለታለመለት ግዙፍ ፕሮጀክት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት የመሬት ጠረጋ (Earthwork) ስራዎችን የሚያከናውነው ኮንትራክተር ወደ ስራ ገብቷል ብለዋል። የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ እ.ኤ.አ በ2030 እንደሚጠናቀቅ ጠቁመው፤ ለዋናው ግንባታ የሚሆኑ ተቋራጮችን የመምረጥ ሂደትም መጀመሩን ተናግረዋል።
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ስርዓት የዘመናት ስብራት ምላሽ የሚሰጥ ነው
Jan 10, 2026 63
አዲስ አበባ፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ስርዓት የዘመናት ስብራት ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል። የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ በሁለት ምዕራፍ የሚከናወን ሲሆን፤ ግንባታው ሲጠናቀቅ በዓመት 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል። የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ 60 ሚሊየን መንገደኞች የማስተናገድ አቅም በመያዝ እንደ አውሮውፓውያን አቆጣጠር በ2030 እንደሚጠናቀቅም ነው የተገለጸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት 80 ዓመታት የጥንታዊ ሀገር ምልክትና ኩራት ሆኖ ስኬታማ ስራ ማከናወኑን ተናግረዋል። አየር መንገዱ በእነዚህ ዓመታት ያለፈባቸው መንገዶች አልጋ በአልጋ እንዳልነበሩ አስታውሰው፤ በኢትዮጵያ ያጋጠሙ የመንግስት ስርዓት መለዋወጥም ሆኑ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳይበግሩት በከፍተኛ ብቃት የአፍሪካ ኩራት መሆን መቻሉንም አብራርተዋል። ከአየር መንገዱ የስኬታማነት ጉዞ ጀርባ ያለው ታላቅ ምስጢር ደግሞ ጠንካራ የኮርፖሬት ባህል መገንባት መቻሉ መሆኑንም አንስተዋል። በዚህም አየር መንገዱ ጥቅሙን ባስጠበቀ መልኩ ያለምንም ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆኖ በዓለም አቀፍ የቢዝነስ ህግ እየተመራ መቀጠሉን ነው የተናገሩት። ለደህንነት ቅድሚያ የሚሰጥ፣ በፈጠራና ትጋት የሚሰሩ አመራሮች፣ በተደመረ አቅም የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በትጋትና ሃላፊነት የሚሸከሙ ሰራተኞች ያሉት መሆኑን አውስተው፤ ተቋሙ ዘወትር ለመማር ዝግጁ መሆኑ ደግሞ አየር መንገዱን ልዩ እንደሚያደርገውም አብራርተዋል። ዛሬ ግንባታው የተጀመረው የአውሮፕላን ማረፊያው በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን በማስተናገድ በዓለም ላይ ካሉ ጥቂት ግዙፍ አውሮፕላን ማረፊያዎች አንዱ እንደሚሆን ተናግረዋል። አዲስ የሚገነባውን አውሮፕላን ማረፊያ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር የሚያገናኝና በአንድ ጊዜ 12 ተሽከርካሪ ማስተናገድ የሚችል የፍጥነት መንገድ እንዲሁም ፈጣን የባቡር መንገድ እንደሚገነባም ገልጸዋል። የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በሰማይ ለሚበሩ መርከቦቻችን እንደ ትልቅ ወደብ ሆኖ ያገለግላል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም ለኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ስርዓት የዘመናት ስብራት ምላሽ የሚሰጥ ስለመሆኑ አብራርተዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ስኬታማ እንደሆነ ሁሉ የሚገጥሙን ፈተናዎች ይበልጥ እንድንተጋ እና ለስኬታችን እንድንጸና ያደርጉናል ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ140 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ያሉት ግዙፍ ኩባንያ ሲሆን፤ በተያዘው እኤአ 2026 ተጨማሪ አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን ወደ ስራ እንደሚያስገባም ይጠበቃል።
አየር መንገዳችን የአፍሪካ አስተሣሣሪነቱን የሚያጸና አዲስ ምዕራፍ ጀምሯል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jan 10, 2026 81
አዲስ አበባ፤ጥር 2/2018 (ኢዜአ)፦ አየር መንገዳችን ለ80 ዓመታት የዘለቀውን የአፍሪካ አስተሣሣሪነቱን የሚያጸና አዲስ ምዕራፍ ጀምሯል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ ጠቅላይ ሚኒስትራችን በጉባ ካበሠሯቸው ሜጋ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነውንና በአፍሪካ ግዙፉን የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ዛሬ በቢሾፍቱ አስጀምረናል ብለዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከስምንት አስርት ዓመታት በፊት በጥቂት አውሮፕላኖች ጉዞውን ጀመረ፤ ዓላማው ኢትዮጵያን ከዓለም ጋር ማገናኘት ብቻ አልነበረም፤ የአፍሪካን ክብር በሰማይ ላይ ከፍ አድርጎ ማሳየት ጭምር እንጂ ሲሉም አብራርተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቢሾፍቱ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን በይፋ አስጀመሩ የቢሾፍቱ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ይሆናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዓመት እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ ዐቅም የሚፈጥረው አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ የኩራት ታሪካችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የኢትዮጵያ ግልጽ ራዕይና የብልጽግና ጉዞ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ የመንግሥታችንን በትልቁ አስቦ በትልቁ የማሳካት ዕይታን የሚገልጥ፣ የአፍሪካን የልዕልና ጉዞ በማረጋገጥ በዓለም አቪዬሽን መሪ ሚና እንዲኖራት የሚያስችል ነው ብለዋል። የአየር መንገዳችንን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ይበልጥ ከፍ የሚያደርገው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ፋይዳው የላቀ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ አየር መንገዱ ወደ አፍሪካ መግቢያ እና መውጫ ዋናው በር ሆኖ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ የፈጠራና ፍጥነት ጉዟችን በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዲጂታላይዝ የሆነ አሰራሩን ማጠናከር ይገባዋል
Jan 10, 2026 79
አዲስ አበባ፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የሪፎርም ስራዎችን በመተግበር አሰራሩን ዲጂታላይዝ በማድረግ የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስገነዘበ። የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ ምክትል ሰብሳቢዎች እና ከምክር ቤቱ ሴቶች ኮከስ አመራር አባላት ጋር ውይይት አካሂዷል። ውይይቱም የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን እያከናወናቸው በሚገኙ የሪፎርም እና የዲጂታል ስራዎች፣ የግዥና ንብረት የህግ ማዕቀፎች እንዲሁም ወደፊት በትኩረት ሊሰራባቸው በታቀዱ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ ፤ ባለስልጣኑ ሪፎርም ስራዎችን በመተግበር አሰራሩን ዲጂታላይዝ በማድረግ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ማጠናከር እንዳለበት ተናግረዋል። ባለስልጣኑ በተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ በመንግስት ግዥና ንብረት ዲጂታላይዜሽን፣ ከዘለቄታዊነት የግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓት በማጎልበት ከመንግስት ግዥና ንብረት አገልግሎት እና መረጃ ጥራትና ሽፋን ለማሳደግ ያከናወነው ስራ ለሌሎችም ተቋማት በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ገልጸዋል። ተቋሙ እየተገበረ በሚገኘው ዘመናዊ አሰራር ከሀገር አልፎ ለሌሎች ሀገራትም ልምድ እያካፈለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በመንግስት ግዥ ውጤታማ እንዲሆንና ግልጸኝነት ያለው አገልግሎት እንዲሳለጥ በማድረግ በኩል እያከናወነ ያለውን ተግባር ሊያጠናክር እንደሚገባ ገልጸዋል። የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ በበኩላቸው፤ ተቋሙ በዘመናዊ አሰራር በመታገዝ የግዥ ስርዓቱን ለማዘመንና የቁጥጥር ስርዓቱን ከማጠናከር አኳያ በርካታ ስራዎች እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ከግዥ ጋር ተያይዞ ያለውን ግልጸኝነት ከማረጋገጥ እና ህገ-ወጥነት ለመከላከል የሚያስችሉ የተለያዩ ዘመናዊ ስርዓቶችን መዘርጋቱን አብራርተዋል። ባለስልጣኑ የአሰራር ስርዓቱን ጥራትና ቅልጥፍና ለማሳደግ አዋጁን፣ መመሪያዎችንና የአሰራር ስርዓቶችን ተግባራዊ በማድረጉ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመዋል። ለተገልጋዮች እና ለባለድርሻ አካላት ተከታታይ ሥልጠና መስጠቱንም ገልጸዋል። በተለይ የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥን (e-GP) ከፌዴራል ተቋማት አልፎ ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የማውረድ ስራዎች ማከናወኑን ጠቁመዋል። በውይይት የተሳተፉና አስተያየታቸውን የሰጡት የተለያዩ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች በበኩላቸው፤ ተቋሙ አሰራሩን ዘመናዊ እና ግልጸኝነት በማስፈን እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ እንደገለጹት፤ ተቋሙ አሰራሩን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የሚያከናውናቸው ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው። የመንግስት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የመንግስት ግዥ ስርዓት ግልጽና ፍትሃዊ እንዲሆን እየተደረገ ያለው የመቆጣጠር ስራ የሚበረታታ መሆኑን ነው የገለጹት። ተቋሙ ከራሱ አልፎ ሌሎች ተቋማትን በዘመናዊ አሰራር ለማዘመን እያደረገ ያለው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን ጠቁመዋል። የመንግስት ልማት ድርጅት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ መለሰ መና በበኩላቸው፤ ባለስልጣኑ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ያደረገው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ገልጸዋል። የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እጸገነት መንግስቱ በበኩላቸው፤ ባለስልጣኑ በምክር ቤቱ የወጡ አዋጆችን በአግባቡ በመተግበር ለሌሎችም ተቋማት ምሳሌ መሆኑን ገልጸዋል። ባለስልጣኑ የጀመረውን ተግባር በማጠናከር ለወደፊት የላቁ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባው አሳስበዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ለጉምሩክ አገልግሎት መቀላጠፍ ትልቅ ዕድል ይዞ መጥቷል
Jan 8, 2026 218
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ቀልጣፋ የጉምሩክ አገልግሎትን ለማጠናከር ትልቅ ዕድል ይዞ መምጣቱን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ዋነኛ ዓላማዎቹ ናቸው። የጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሙሉ ወርቅ ደረሰ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኮሚሽኑ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትግበራ ወቅት የንግድ እንቅስቃሴን የሚያሳልጡ፣ ኮንትሮባንድን ለመቆጣጠር የሚያስችሉና በአጠቃላይ የኮሚሽኑን ስራዎች የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎች ወደ ሥራ አስገብቷል። ቴክኖሎጂዎቹ ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን ክትትል ለማጠናከር፣ የሰው ንክኪና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል እንዲሁም ደንበኞች ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ደግሞ በጉምሩክ ዘርፍ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማዘመን እና ለማቀላጠፍ ትልቅ እድል ይዞ መምጣቱን ጠቅሰዋል። ስትራቴጂውን ስኬታማ ለማድረግ የተቋማት ቅንጅት እንደ ዋነኛ የድጋፍ ማዕቀፍ መሆኑን በማንሳት፥ ኮሚሽኑ የበከሉን ይወጣል ብለዋል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ አሰራር ተግባራዊ መደረጉን ገልጸው፤ በሂደት ላይም ያሉ ቴክኖሎጂዎች በቀጣይ ወደ ስራ ይገባሉ ብለዋል። ምክትል ኮሚሽነሯ እንደገለጹት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የጉምሩክ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የማድረግ ሰራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
የኢትዮጵያ ሳተላይቶች ያመነጯቸው መረጃዎች ጉልህ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አበርክተዋል
Jan 8, 2026 126
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሳተላይቶች ያመነጯቸው መረጃዎች ጉልህ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማበርከታቸውን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ገለጸ። በሚቀጥለው ዓመትም ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ የመረጃ ሳተላይት ወደ ሕዋ ለማምጠቅ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል። የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን ሳተላይት ኢቲ-አር.ኤስ.ኤስ1 (ET-RSS1) እንዲሁም ሁለተኛው ኢቲ-ስማርት-አር.ኤስ.ኤስ (ET-SMART-RSS) የተሰኙ ሁለት የመረጃ ሳተላይቶችን ወደ ሕዋ ማምጠቋ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ቀደም ሲል ወደሕዋ የተላኩ ሁለት የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች የአገልግሎት ጊዜያቸውን አጠናቀዋል። የመሬት ምልከታ የመረጃ ሳተላይቶቹም በርካታ ቴክኖሎጂያዊና ሳይንሳዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን ማበርከታቸውን ተናግረዋል። በዚህም የምግብ ዋስትና፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በተፈጥሮ ሃብት አያያዝ የግብርና መስኮች፣ በከተማ ፕላንና መሠረተ ልማት፣ በሀገር ሉዓላዊነትና ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ጠቀሜታ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም በሚቀጥለው ታኅሳስ 2019 ዓ.ም በምስል ጥራትና የጊዜ ቆይታ አቅም ያላት ኢቲ-አር.ኤስ.ኤስ 2 (ET-RSS2) የተሰኘች ሳተላይት ወደ ሕዋ ለማምጠቅ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። በቀጣይ የምትመጥቀው ኢቲ-አር.ኤስ.ኤስ 2 ሳተላይት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመታጠቅ በሕዋ ላይ የአምስት ዓመታት የጊዜ ቆይታ እንዲኖራት ታሳቢ መደረጉ ነው የተገለጸው። ከዚህ ቀደም ወደ ሕዋ ከተላኩ ሳተላይቶች የተገኘውን መረጃ የመቀበል፣ የመተንተን፣ የመቆጣጠርና የጥገና አቅም መፈጠሩን አስረድተዋል። ሦስተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ እየተደረገ የሚገኘው ጥረትም የኢትዮጵያን የሳተላይት ልማት አቅም በተግባር የሚያሳይ እንደሚሆን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረት እየጣለች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jan 6, 2026 179
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የፖሊሲ ማዕቀፍ እና መሰረተ ልማትን ጨምሮ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረት የሚጥሉ ስራዎችን እያከናወነች እንደምትገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በማስመልከት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሑፍ አቅርበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ ከምሁራን ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤ.አይ) በዓለም ደረጃ ያለው ተጽእኖ እና ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። በተጠናቀቀው የ2025 የፈረንጆቹ ዓመት ኤ.አይ በርካታ ስራዎችን መተካቱን አውስተው አሁንም በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ፈጥነን ልጆቻችንን ካዘጋጀን ሰው ሰራሽ አስተውሎትን እንደ ተለያዩ ምርቶች በቀላሉ መጠቀም እንችላለን ብለዋል። ኤ.አይ ስራ ይቀማል ብዬ አልሰጋም ሲሉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሰው ልጅ መስራት የሰው ልጅ ሊሰራቸው የማይገባቸውን ስራዎች እየተካ ይሄዳል ነው ያሉት። ኤ.አይን የምንፈጥር እኛነን ኤ.አይን የምንቀይር እኛ ነን ቀድመን ግን ፋውንዴሽን መጣል ይገባናል ብለዋል። መንግስት ለሰው ሰራሽ አስተውሎት ፖሊሲ እና ስትራቴጂ አዘጋጅቶ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው ሳይንስ ሙዚየም አንዱ መሰረተ ልማት መሆኑን ተናግረዋል። መሰረተ ልማት እና ታለንት ለዘርፉ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱም ነው ያብራሩት። ኢትዮጵያ የምትገነባው የኤ.አይ ዩኒቨርሲቲም የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን ብዙ ችግሮች ይፈታል ተብሎ እንደሚታመን ተናግረዋል። ዋናው ለልጆቻችን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልጆቻችን የሚወዳደሩበት ልጆቻችን ከሌላው አንስው የማይታዩበት ሁኔታ ለመፍጠርም እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ቀድሞ መወዳደር ቀድሞ መገኘት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ኤ.አይን በዛ መልክ ማየት እንደሚገባ ገልጸዋል። ኤ.አይ ስራዎችን በማቃለል እና ጊዜ በመቆጠብ ወሳኝ ድርሻ እንደሚወጡም ነው የገለጹት። ተማሪዎችም ኤ.አይን መጠቀም አለባቸው፤ ቴክኖሎጂዎቹን መጠየቅ እንዲችሉ አድርገን ከፈጠርናቸው ተማሪዎች ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉ ገልጸዋል። የመጠየቅ ብቃት ችሎታ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ረገድም ኤ.አይ የተማሪዎችን አቅም እንደሚገነባ ተናግረዋል። የመጀመሪያው ትውልድ ለኢኮኖሚ ቅድሚያ የሰጠ እና ሁለተኛው ትውልድ ፖለቲካዊውን ያስቀደመ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሁኑ ዘመን የሀሳብ ትውልድ እንደሆነም ጠቅሰዋል። ሀሳብ የሚወድ ትውልድ ችግሮች እየፈታ እና እያቀለለ እንደሚሄድም ተናግረዋል። ኤ.አይ ዝግጅት እና ስራ እንደሚፈልግ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከመፍራት ይልቅ እውነታውን በመጋፈጥ ማሸነፍ እንችላለን ብለዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ በዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች
Jan 10, 2026 31
አዲስ አበባ፤ ጥር 2 /2018 (ኢዜአ)፦ 46ኛው የዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ማምሻውን በአሜሪካ ፍሎሪዳ ተካሄዷል። ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በአምስት ርቀቶች በሁለቱም ጾታዎች በአጠቃላይ 20 አትሌቶችን አሳትፋለች። 10 ኪሎ ሜትር አዋቂ ወንዶች፣ 10 ኪሎ ሜትር አዋቂ ሴቶች፣ ከ20 ዓመት በታች ወንዶች 8 ኪሎ ሜትር፣ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች 6 ኪሎ ሜትር እና ድብልቅ ሪሌይ (4 በ 2 ኪሎ ሜትር) ኢትዮጵያ የተሳተፈችባቸው ርቀቶች ናቸው። የዛሬ ውድድሮችን ተከትሎ ኢትዮጵያ በሶስት የወርቅ፣ ሁለት የብር እና ሁለት የነሐስ በድምሩ ሰባት ሜዳሊያዎችን በማግኘት ኬንያን ተከትላ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ከ20 ዓመት በታች ሴቶች የስድስት ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት ማርታ ዓለማየሁ በ18 ደቂቃ 52 ሴኮንድ አንደኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ በሻምፒዮናው የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች። ኢትዮጵያ በአዋቂ የ10 ኪሎ ሜትር ወንዶች እና ሶሴቶች በቡድን ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችን አግኝታለች። በአዋቂ 10 ኪሎ ሜትር ወንድ ፍጻሜ አትሌት በሪሁ አረጋዊ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አግኝቷል። አትሌት ወሰኔ አሰፋ ከ20 በታች ሴቶች የስድስት ኪሎ ሜትር ውድድር ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች። በ10 ኪሎ ሜትር ሴቶች አትሌት ሰናይት ጌታቸው እና በድብልቅ ሪሌይ (ዱላ ቅብብል) የነሐስ ሜዳሊያዎች ተገኝተዋል። ኬንያ ሶስት የወርቅ፣ አራት የብር እና ሁለት የነሐስ በድምሩ ዘጠኝ ሜዳሊያዎችን በማግኘት አንደኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ዩጋንዳ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። አውስትራሊያ፣ ፈረንሳይ፣ ጃፓን እና አሜሪካ ሌሎች ሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ የገቡ ሀገራት ናቸው። ኢትዮጵያ በሻምፒዮና ተሳትፎ ታሪኳ የዘንድሮውን ጨምሮ 112 የወርቅ፣ 123 ብር እና 67 የነሐስ በድምሩ 302 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከኬንያ በመቀጠል ስኬታማዋ ሀገር ናት። ኬንያ የዘንድሮውን ጨምሮ ኬንያ 160 ወርቅ፣ 114 የብር እና 80 የነሐስ በድምሩ 354 ሜዳሊያዎችን በማግኘት የበላይነቱን ይዛለች።
ናይጄሪያ ለግማሽ ፍጻሜ አለፈች
Jan 10, 2026 52
አዲስ አበባ፤ ጥር 2 /2018 (ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሶስተኛ የሩብ ፍጻሜ መርሃ ግብር ናይጄሪያ አልጄሪያን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በማራካሽ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ቪክቶር ኦሲሜን በ47ኛው እና አኮር አዳምስ በ57ኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ኦሲሜን በውድድሩ ላይ ያስቆጠራቸውን ግቦች ብዛት ወደ አራት ከፍ በማድረግ በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክሩ አምስት ግቦች ያለውን የሞሮኮውን ብራሂም ዲያዝ ተከትሎ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በጨዋታው ላይ ናይጄሪያ በተጋጣሚዋ ላይ ከፍተኛ ብልጫ ወስዳለች። ንስሮቹ ተጨማሪ ግቦችን ለማስቆጠር የሚችሉባቸውን እድሎች አልተጠቀሙም። ውጤቱን ተከትሎ ናይጄሪያ ግማሽ ፍጻሜ የገባች ሶስተኛ ሀገር ሆናለች። በግማሽ ፍጻሜው ከአዘጋጇ ሞሮኮ ጋር የምታደርገው ጨዋታ ከወዲሁ ተጠባቂ ነው። ምሽት አራት ሰዓት ላይ የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቯር ከግብጽ በአጋዲር ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።
ማንችስተር ሲቲ ኤክስተር ሲቲን 10 ለ 1 በማሸነፍ በኤፍኤ ካፕ ቀጣዩን ዙር ተቀላቀለ
Jan 10, 2026 52
አዲስ አበባ፤ ጥር 2 /2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ኤፍኤካፕ የሶስተኛ ዙር መርሃ ግብር ማንችስተር ሲቲ ኤክስተር ሲቲን 10 ለ 1 ረቷል። ማምሻውን በኢትሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሮድሪ፣ ራያን ማይካዶ፣ ማክስ አሊይን፣ ሪኮ ሉዊስ፣ አንቶዋን ሴሜንዮ፣ ናታን አኬ፣ ቲጃኒ ራይንደርስ፣ ኒኮ ኦራይሊ እንዲሁም የኤክስተሮቹ ጃክ ፊትዝዋተር እና ጃክ ዶይል-ሄይስ በራሳቸው ላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጆርጅ ቢርች ለኤክስተር ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ከቦርንማውዝ የፈረመው አንቶዋን ሴሜኒዮ የመጀመሪያ ጎሉን ለሲቲ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ ወደ አራተኛ ዙር አልፏል።
ኢትዮጵያ መድን ወደ አሸናፊነት ተመልሷል
Jan 10, 2026 49
አዲስ አበባ፤ ጥር 2 /2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 14ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮጵያ መድን ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በረከት ካሌብ እና ብሩክ ሙሉጌታ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ቴዎድሮስ ኃይለማርያም ለወላይታ ድቻን ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከአምስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ኢትዮጵያ መድን በ16 ነጥብ ደረጃውን ከ16ኛ ወደ 15ኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ አራተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በውድድር ዓመቱ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወላይታ ድቻ በ12 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ጨዋታውን ተከትሎ የ14ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የ5ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ በልዩ ትኩረት ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ ነው
Jan 10, 2026 61
መቱ፤ ጥር 2/2018 (ኢዜአ)፡- በኢሉአባቦር ዞን በልዩ ትኩረት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን የዞኑ የግብርና ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አወል መሐመድ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በያዝነው የበጋ ወራት በዋናነት የተቀናጀ የአፈርና ውኃ ጥበቃን ጨምሮ ችግኝ የማዘጋጀት ሥራ እየተሠራ ነው። በዚህም መሠረት 131 ሺህ ሔክታር መሬት የሚሸፍን የተፋሰስ ልማት ሥራ ሕብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። የተፋሰስ ልማት በተሠራባቸው አካባቢዎች የሚተከሉ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው በርካታ ችግኞች እየተዘጋጁ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ችግኞቹ ለምግብነት፣ ለደን ልማት፣ ለከብቶች መኖና ለውበት የሚውሉ መሆናቸውንም ነው ያብራሩት። የችግኝ ዝግጅቱ በመንግሥት ችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች እና በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ መካሄዱንም አስረድተዋል። በመጪው ክረምት የሚተከሉ ችግኞች ከአካባቢ ጥበቃ ፋይዳ ባለፈ በችግኝ ማፍላት ለሚሳተፉ ወገኖች የሥራ እድል እንደፈጠሩመ አክለዋል። በችግኝ ማፍላት ሥራው የሥራ እድል ከተፈጠረላችው መካከል ሽብሩ አምቢሳ እንዳሉት፤ በችግኝ ጣቢያዎች ተቀጥረው ከሚያገኙት ገቢ ባሻገር በሥራው ያገኙትን ልምድ በግል ማሳቸው ላይ ለማስፋት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ችግኞችን ከማዘጋጀት ሥራ ጎን ለጎን ባለፈው ክረምት የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ሥራም እያከናወኑ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር መተግበር ከጀመረ ወዲህ ችግኝ በማዘጋጀት ገቢ እያገኙበት መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አበራ ገለታ ናቸው።
በሐረሪ ክልል በተፋሰስ ልማት የተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ምርትና ምርታማነትን አሳድጓል
Jan 10, 2026 56
ሐረር፤ ጥር 2/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ባለፉት ዓመታት በተፋሰስ ልማት የተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ምርትና ምርታማነት ማሳደጉን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር ገለጹ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሃላፊ ሮዛ ኡመር፤ የዘንድሮውን የክልሉን የተፋሰስ ልማት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በዛሬው እለት አስጀምረዋል። በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ተጨባጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አንስተው ዘንድሮም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በተለይም የከርሰ ምድር ውሃን በማጎልበትና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል። የክልሉ የተፈጥሮ ሀብት ልማት አጠቃቀም እና ጥበቃ ዳይሬክተር አራርሶ አደም፤ በክልሉ በዘንድሮ በጋ ወራት 9 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እንደሚከናወን ተናግረዋል። በዚህም 300 ሄክታር በሚሆን መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው እንደሚከናወን ጠቁመው በተፋሰስ ልማት ስራው ከ11 ሺህ በላይ ሰዎች ይሳተፋሉ ብለዋል። በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የለሙ ተፋሰሶች የጎርፍ ተጋላጭነትን ከመቀነስ ባለፈ ለወጣቶች የስራ ዕድል እንደፈጠረም ገልጸዋል።
የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራን በብቃት በማከናወን ለከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት ማድረግ ተችሏል
Jan 10, 2026 63
አዲስ አበባ፤ ጥር 2/2018 (ኢዜአ)፦ የመዲናዋን ወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራ በብቃትና በልቀት በማከናወን ለከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት ማድረግ መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ እየተገነቡ ከሚገኙ ስምንት የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች መካከል የቀበና እና የግንፍሌ ወንዞችን የመስክ ምልከታ በማድረግ የሥራ ሂደቱን ገምግመዋል። ከንቲባዋ በጉብኝታቸው ወቅት እንደገለጹት፤ የከተማዋ የወንዝ ዳርቻዎች ቀደም ሲል በቆሻሻ ክምችት የተሞሉ፣ በከባድ ጠረን ምክንያት ለመጠጋት የማይቻልበት ስፍራዎች ነበሩ። ሆኖም አሁን ላይ ይሄ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ተቀይሮ አካባቢው ውበት ተጎናፅፎ ለከተማችን ትልቅ የቱሪስት መዳረሻ ሆኗል ብለዋል። ነዋሪዎች ንጹህ አየር የሚያገኙበት እና የሚዝናኑበት ምቹ አካባቢ መፈጠሩን አክለው ተናግረዋል። ቀደም ሲል ለሕገ-ወጥ ተግባራት መሸሸጊያ የነበሩ ስፍራዎች አሁን ላይ ወደ ልማት በመቀየራቸው የነዋሪዎች ደህንነት መረጋገጡን ጠቁመዋል። የወንዝ ዳርቻ ልማቱ በኢትዮጵያ አዲስ የልማት አይነት መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባዋ፤ ሥራው በብቃትና በልቀት እየተከናወነ ነው ብለዋል። ፕሮጀክቱ ለበርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን የጠቀሱት ከንቲባዋ፤ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል እና አካባቢን በመጠበቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ነው ያሉት። ደርቀው የነበሩ ምንጮች ዳግም መፍለቅ መጀመራቸውን አንስተው ልማቱ ተጨባጭ ውጤት እየታየበት መሆኑ ከንቲባዋ ጠቅሰዋል። የወንዝ ዳርቻ ልማት ለሀገራችን አዲስ ተሞክሮ መሆኑን ጠቅሰው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ አስደናቂና ለውጥ አምጭ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። የወንዝ ዳርቻ ልማቱን ተከትሎ ባለሀብቶች በአካባቢው የተለያዩ ኢንቨስትመንቶችን እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርበዋል። የብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የቀበና ግንፍሌ ፒኮክ ፓርክ ወንዝ ዳርቻ ልማት የሚያስተባብሩት አቶ ሞገስ ባልቻ በበኩላቸው፤ አካባቢው ለረጅም ጊዜ በተለያየ መልኩ ሳይጠቅም የባከነና ትኩረት ተነፍጎት የቆየ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም አሁን ላይ በተከናወነው የተቀናጀ የጽዳትና የውበት ስራ ስፍራው ዳግም ህይወት ዘርቶ ለከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት እንደሆነ ገልጸዋል። ይህም በቆሻሻ ተሸፍኖ የነበረውን እምቅ አቅም እንዴት ወደ ትልቅ ተስፋ መቀየር እንደሚቻል በተግባር የታየበት መሆኑን ተናግረዋል። ለነዋሪዎች ምቹ፣ ለጎብኚዎች ማራኪ የመዝናኛ ስፍራ መሆኑን በማንሳት ለከተማዋ ደግሞ አዲስ የኢኮኖሚና የውበት ምንጭ እንደሆነ ገልፀዋል። ይህ ስራ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባሻገር የማይቻሉ የሚመስሉ ነገሮችን በትጋትና በቅንጅት ወደ ትልቅ ውጤት መቀየር እንደሚቻል ትልቅ ትምህርት የሰጠ መሆኑንም ነው አቶ ሞገስ የገለጹት።
በመዲናዋ እየተገነባ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት አዲስ የልማትና የግንባታ እሳቤን ዕውን ያደረገ ፕሮጀክት ነው
Jan 9, 2026 111
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ እየተገነባ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት አዲስ የልማትና የግንባታ እሳቤን ዕውን ያደረገ ዘላቂ ልማትን ማረጋገጫ ፕሮጀክት መሆኑን አዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ፡፡ ፕሮጀክቱ የተፈጥሮ ሃብት ህልውናን በመጠበቅ የከተማዋን ገጽታና ደረጃ ለማሳደግም አይነተኛ አበርክቶ ያለው መሆኑን ከንቲባዋ ጠቁመዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤በአዲስ አበባ ከተማ እየተገነቡ ከሚገኙ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች ውስጥ የቀበናና ግንፍሌ ወንዞች ልማት ሂደትን ገምግመዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ ወንዞቹና ዳርቻዎቻቸውን ከስጋትነት አላቆ የተሻለ የከተማ ስነምህዳርና ገጽታ ያላበሰ የዛሬ ትውልድ ታላቅ አሻራ ነው ብለዋል ከንቲባዋ፡፡ እነዚሁ ፕሮጀክቶችም የአዲስ አበባን ስነምህዳር በዘላቂነት እንዲጠበቅ ከማድረግ አልፈው የነገ የከተማዋ ፍላጎትና የቤት ስራዎችን ታሳቢ ያደረጉ ተጨማሪ ልማቶችን ያካተቱ መሆናቸውንም ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል፡፡ ፊት የማይሰጣቸውና ለልማት የተገለሉ የነበሩ የወንዝ ዳርቻዎች ዛሬ ላይ የብዙዎች አይን ማረፊያ ምቹ የአገልግሎት መስጫ ማእከላት ሆነው መልማታቸውን የገለፁት ከንቲባዋ አልሚዎችና ባለሃብቶች እነዚህን የለሙ ስፍራዎች ይጠቀሙባቸው ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ለአዲስ አበባም ለሀገርም አዲስ ደግሞም ምሳሌ የሆነው ወንዝ ዳርቻ ልማት የከተማዋን ህልውና በጽኑ መሰረት ላይ ለማኖር የከተማዋን ከስሟ የመስተካከል ትጋትን ለማሳለጥ የሚያግዝ ውጤት እየተገኘበት ስለመሆኑ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል፡፡ 8 ዋና ዋና የአዲስ አበባ ወንዞችን ያቀፈው 48 ኪሎሜትር የሚሸፍነው የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ግንባታ እየተጠናቀቀ መሆኑን ያስታወቁት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የግንባታ ሂደቱን እያስተባበሩ ላሉ አመራሮች በግንባታው እየተሳተፉ ላሉ ሰራተኞች እንዲሁም ድጋፍ እያደረጉ ላሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በከተማዋ እየተገነቡ ካሉ 8 የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች ውስጥ አንዱ የሆነውን የቀበና ግንፍሌ ፒኮክ ፓርክ ወንዝ ዳርቻ ልማት የሚያስተባብሩት የብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ፤ ከእንጦጦ ተራራ ተነስቶ ቁልቁል ከተማዋን እየከፈለ በሚሄደው የቀበና ወንዝ ዳርቻ እየተጠናቀቀ ያለው ልማት ከውሃ ሃብት ጥበቃ ስራ ባሻገር ተጨማሪ አገልግሎት መስጫ የገቢ ማስገኛ አማራጮች ያሉት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት ትላንት የሚያስቆጭ ነገን የሚያስናፍቅ ብርታትና ተስፋን የሚያሰንቅ ነው ብለዋል የብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊው አቶ ሞገስ፡፡ የአዲስ አበባ ወንዝ ተጎራባች ስፍራዎች ለተፈጥሮ ሃብቱ ስጋት ሆነው ለዘመናት ከመዝለቃቸው በላይ ለነዋሪዎቹ የሰቀቀን ህይወትን ለመግፋት ሰበብ የነበሩ መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ ዛሬ ላይ በወንዝ ዳርቻ ልማት ተፈጥሮም ህይወትም ዳግም ህይወት ዘርተዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የቻይና አፍሪካ ትብብር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል
Jan 8, 2026 102
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማሕሙድ አሊ ዩሱፍ ከቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ጋር ውይይት አካሄዱ። ውይይቱ እያደገ የመጣው የቻይና አፍሪካ ትብብርን ማጠናከር ላይ ያለመ ነው ተብሏል። ቻይና የአፍሪካ እውነተኛ አጋር መሆኗን የገለፁት የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ያተኮረው ፖሊሲ ጠንካራ ወዳጅነት እንዲፈጠር ማድረጉን ገልፀዋል። የቻይና አፍሪካ ግንኙነት በተለያዩ የትብብር ማዕቀፎች እያደገ መምጣቱንም ተናግረዋል። ከውይይቱ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ሁለቱ ወገኖች የዓለም ደቡባዊ ቀጣና (Global South) ሀገራትን መብትና ጥቅም ለማስከበር፣ የሉዓላዊነትን ክብር ለመጠበቅ እና ዓለም አቀፍ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በጋራ ለመሥራት መስማታቸውን አስታውቀዋል። በውይይቱ ወቅት የቻይናን የአምስት ዓመት የልማት ዕቅድ ከአፍሪካ ኅብረት የ2063 አጀንዳ ሁለተኛው የዐሥር ዓመት ትግበራ ጋር በማጣጣም ዘመናዊነትን ለማምጣት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ምክክር መደረጉ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነቶችን ጨምሮ፣ ቻይና ያቀረበቻቸውን ዓለም አቀፍ የደኅንነትና የልማት ተነሳሽነቶች በጋራ ለመደገፍ ከስምምነት መድረሳቸውን ኢቢሲ ዘግቧል። በተጨማሪም የተፈረሙ የትብብር ስምምነቶችን በተግባር በመተርጎም እና የንግድ ልውውጥን በማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት በጋራ መግለጫቸው አረጋግጠዋል።
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ በቀጣዩ ሳምንት ይጀመራል
Jan 8, 2026 116
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ(PRC) መደበኛ ስብሰባው ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ያተኮረ ነው። በስብሰባው የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብሰባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብሰባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት፤ የአፍሪካ ህብረት የ2026 መሪ ሀሳብ ዋና የትኩረት አጀንዳ
Dec 26, 2025 615
39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ነው። መሪ ሀሳቡን ያረቀቀው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የዘንድሮው መሪ ቃል ከአጀንዳ 2063 ጋር የተቆራኘ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። ሁሉም አፍሪካዊ ንጹህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በቂ ውሃ ለመጠጥ፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና ለሌሎች ፍላጎቶቹ እንዲያገኝ የማድረግ ራዕይን ለማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል። ህብረቱ የውሃ ደህንነት እንደ አህጉር የተያዙ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን በማዕቀፎቹ አስቀምጧል። ውሃ እና ንጽህና የኢኮኖሚ እድሎችን በማስፋት፣ የስራ አጥነት ምጣኔን በመቀነስ፣ የስደቶችና ተፈናቃዮችን ጫና ለማቃለል እንዲሁም ለሰላምና ደህንነት መስፈን አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተመላክቷል። የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ህብረቱ ውሃ እና ንጽህና ለጤና፣ ለኢኮኖሚ እድገት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥና ዘላቂ የአካባቢ ምህዳር ለመፍጠር መሰረት መሆኑን የበለጠ እውቅና እንደተሰጠው አመልክቷል። ሁሉን አቀፍ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይገበር የውሃ ደህንነትን የማረጋገጥ አላማ ካለው የአፍሪካ የውሃ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው። የዘንድሮው መሪ ቃል የአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ጥረቶችን ያስተሳሰረ ድልድይ ሆኗል። በዘላቂ ልማት ግቦች ውስጥ ያለው ግብ ስድስት ከውሃ እና ንጽህና ጋር የተያያዘ ነው። ይህ ግብ እ.አ.አ በ2030 ለሁሌም ዜጋ ደህንነቱ የተረጋገጠ ውሃ አቅርቦትና የንጽህና አጠባበቅን ተደራሽ የማድረግ አላማ አለው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት በፍጥነት መስፋፋትና ውሃ በአግባቡ አለመጠቀም የውሃ ደህንነት እና ዘላቂ አቅርቦት ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። የንጽህና አጠባበቅ የአፍሪካ አንዱ ፈተና ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች መሰረታዊ የሚባል የንጽህና መጠበቂያ መሰረተ ልማቶችን አያገኙም። ይህም እንደ ኮሌራ ላሉ የውሃ ወለድ በሽታዎች መስፋፋት ምክንያት ሆኗል። የተቀናጀ የውሃ አስተዳደር ስርዓት፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ ለዘላቂ መሰረተ ልማት የሚፈሰወን መዋዕለ ንዋይን ማሳደግ፣ ውሃ በድጋሚ አጣርቶ መጠቀም፣ የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ፣ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር እና ለውሃ ደህንነት ትኩረት የሚሰጡ ፖሊሲዎችና ማዕቀፎችን በውጤታማነት መተግበር ያሉትን እድሎች በዘላቂነት ለመፍታትና ፈተናዎችን ለመቅረፍ ያስችላል። ደህንነቱ የተረጋገጠ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ላይ ያለፈውን ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የቆሸሸ ውሃ በአግባቡ ማከም፣ የንጽህና አጠባበቅ ማስፋትና የግንዛቤ ፈጠራ ስራን በስፋት ማከናወን፣ ማህበረሰብ መር የንጽህና አጠባበቅ ኢኒሼቲቮችን ትግበራ ማስፋት፣ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎችና ሀገር በቀል አቅምን መገንባት ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓትን መፍጠር ያስችላል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና ጤናማ ማህበረሰብ ግንባታ ያላቸውን ቁልፍ ሚና የሚያሳይ ነው። የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ማድረግ መሰረታዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ ለማህበረሰብ ደህንነትና የተሻለ የኑሮ ዘይቤ፣ ለአካባቢ ጥበቃና ለአፍሪካ ብልጽግና መረጋገጥ ስትራቴካዊ አቅም ናቸው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በሚካሄድበት ወቅት በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም እና 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኞች ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳሉ። ኢትዮጵያ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የአፍሪካ ጣሊያን ስብሰባን ለማዘጋጀት ብሄራዊ የዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቀን ነው - የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Dec 24, 2025 524
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ሲል የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ገለጸ። የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በኤርትራ መንግሥት አገዛዝ ደረሰብን ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ጋምቢያ(ባንጁል) የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ላቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን አድንቋል። በኤርትራ መንግስት ላይ የቀረቡትን ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክስ ተቀብሎ በመዝገብ ቁጥር 868/25 መመዝገቡን፣ የክሱ ፍሬ ነገር እና ይዘት ተቀባይነት ያለው መሆኑን እውቅና በመስጠት የኤርትራ መንግስት እንዲመልስ ክሱን መላኩን ኮሚሽኑ ማስታወቁን ገልጿል። የድርጅቱ ሊቀ-መንበር ኢብራሂም ሀሩን በመግለጫቸው እንደተናገሩት፤ የኤርትራው መንግሥት በደናክል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ህዝቦች እየፈፀመ ያለው መጠነ ሰፊ፣ ስልታዊ፣ መንግስታዊ መር እና ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በአሁኑ ወቅት እየደረሱ ነው ካሏቸው የመብት ጥሰቶች መካከልም ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ማካሄድ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት፣ በሺዎች የሚቆጠሩትን መሰወር፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ማከናወን መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰው፤ በተለይም ከ300ሺህ በላይ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማፈናቀል እና ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል፣ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋትና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን መጣስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ድርጅቱ የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ከ1993 ጀምሮ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰባቸው ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ክስ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እኤአ ጁን 04 ቀን 2025 በ122 ገጽ የተደራጀ ክስ ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የኤርትራ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን እንደገለጸላቸው ጠቁመዋል። ለክሱም ከተጠቀሙት ማስረጃዎች መካከል በድርጅቱ የተከናወነ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ግኝት፣ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝባዊ መብቶች በኤርትራ ላይ የተደረጉ ምርመራዎች፣ ግኝቶችና ማስረጃዎች፣ የመብት ጥሰት የደረሰባቸው የቀይ ባሕር አፋር ተጎጂ ወገኖች እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የተገኙ የሰብዓዊ መብት ምርመራዎችን መቅረቡን ተናግረዋል። ድርጅቱ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት መከራ ለማዳን፣ የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ድምፅ እንዲሆኑት፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡንና የኢሳያስ መንግስት ላይ ህጋዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 446
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 425
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 643
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 798
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 409
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 376
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 1042
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3383
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 2978
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1894
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7713
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6194
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
አማድ ዲያሎ - የአፍሪካ እግር ኳስ ብሩህ ተስፋ
Jan 9, 2026 168
ተጫዋቹ አዲሱ ሳሙኤል ኤቶ የሚል ስያሜ እየተሰጠው ይገኛል። ፍጥነቱን ከዲዲየር ድሮግባ ጋር ያነጻጽሩታል። ለተጋጣሚ ተጫዋቾች የራስ ምታት እና ፈተና የሆነውን ግራ እግሩን ከሌላኛው የግራ እግር ምትሃተኛ ሪያድ ማህሬዝ ጋር የሚያወዳድሩም አልጠፉም። በዚህ አካሄዱ ከቀጠለ ያለ ምንም ጥርጥር ወደፊት በእግር ኳስ ከምንመለከታቸው ኮከቦች አንዱ ሊሆን ይችላል እየተባለለት ይገኛል። ይህ ተጫዋች በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ዓመታት ታሪክ ሀትሪክ የሰራ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ተጫዋች ነው። እያወራን የምንገኘው የማንችስተር ዩናይትድ 16 ቁጥር ማልያ ለባሽ አማድ ዲያሎ ነው። የ23 ዓመቱ ኮትዲቯራዊ ተስፈኛ ተጫዋች በቀያዮቹ ሴጣኖች እያሳየ ያለው ብቃት ከብዙዎች ዘንድ ሙገሳ አስችሮታል፣ አድናቆት እንዲጎርፍለት አድርጓል። ወደ ኋላ መለስ እንበልና የአማድ ዲያሎን መነሻ እንመልከት። ካሜሮን ከአዘጋጇ ሞሮኮ ለግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው አማድ የተወለደው እ.አ.አ ጁላይ 11 2002 በኮትዲቭዋር መዲና አቢጃን ነው። ተጫዋቹ በአፍሪካ ምድር ቢወለድም ገና በህጻንነት እድሜው ነበር ወደ ጣልያን የተሰደደው። የእግር ኳስ ህይወቱን የጀመረው እ.አ.አ በ2014 በጣልያን ሬጂዮ ኢሚሊያ ግዛት በሚገኘው ቦካ ባርኮ የታዳጊ ቡድን ነው። ቡድኑን በተቀላቀለበት ዓመት የገና በዓል (ክሪስማስን) በማስመልከት በተካሄደ ውድድር ላይ በ12 ዓመቱ ኮከብ ግብ አግቢ ሲሆን ያሳየው አስደማሚ ብቃት የብዙዎችን ቀልብ ሳበ። ይህ የገና በዓል ውድድር አማድን እ.አ.አ በ2015 በቦካ ባርኮ ቡድን እንዲመዘገብ አደረገው። ተጫዋቹ በቡድኑ ብዙም አልቆየም። የበርካታ የጣልያን ሴሪአ ክለቦች አይን አረፈበት። ብዙም ሳይቆይ በዛው በ2015 ወደ ጣልያኑ አትላንታ አመራ። አማድ ከእ.አ.አ 2015 እስከ 2019 ለአትላንታ ታዳጊ ቡድን የተጫወተ ሲሆን እ.አ.አ 2019 እና 20 ለዋናው ቡድን ተጫውቷል። ለዋናው ቡድን አራት ጨዋታዎችን አድርጎ ማስቆጠር የቻለው አንድ ግብ ብቻ ነው። የእንግሊዙ ክለብ ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹ በጣልያኑ ክለብ ባሳየው ብቃት በ18 ዓመት እድሜው እ.አ.አ ጃንዋሪ ወር 2021 በአምስት ዓመት ኮንትራት በ37 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዩሮ አስፈርሞታል። ተጫዋቹ ወደ ማንችተር ሲመጣ ቀጥታ ወደ ዋናው ቡድኑ አልተቀላቀለም። በቡድኑ ከ23 ዓመት በታች ጨዋታውን ማድረግ ጀመረ። አማድ የመጀመሪያ ጨዋታውን ለማንችስተር ያደረገው እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 18 2021 ቡድኑ ከሪያል ሶሲዬዳድ ጋር ባደረገው የዩሮፓ ሊግ ጨዋታ ነው። በዛው ዓመት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እና አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ላይ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ዲያሎ ከእ.አ.አ 2022-2023 ባለው ጊዜ ሬንጀርስ እና ሰንደርላንድ በውሰት የተጫወተ ሲሆን በቡድኖቹ ባደረጋቸው 47 ጨዋታዎች 16 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023/24 አማድ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ በመመለስ በድጋሚ መጫወት ጀምሯል። በክለቡም ድንቅ ብቃቱን እያሳየ መምጣት ጀመረ። እ.አ.አ ጥር 17 2025 ማንችስተር ዩናይትድ ከሊጉ ከወረደው ሳውዝሃምፐን ጋር በነበረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር በ12 ደቂቃ ውስጥ ሶስት ግቦችን አስቆጥሮ ሀትሪክ በመስራት ቡድኑ 3 ለ 1 አንዲያሸንፍ ያደረገበት መንገድ አድናቆት አስችሮታል። በዚህም አማድ በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ታሪክ የመጀመሪያ ሀትሪክ የሰራ አፍሪካ ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። አማድ በቀያዮቹ ሴጣኖች ማልያ እስከ አሁን ባደረጋቸው 53 ጨዋታዎች 11 ግቦችን አስቆጥሯል። ተጫዋቹ ከክለቡ በተጨማሪ ለኮትዲቯር ብሄራዊ ቡድን በመጫወት ላይ ይገኛል። እ.አ.አ 2021 ኮትዲቯር ከኒጀር ጋር ባደረገችው ጨዋታ በ86ኛው ደቂቃ ተቀይሮ በመግባት ለብሄራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ለሀገሩ እስከ አሁን ባደረጋቸው 15 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። የመጀመሪያ ጎሉን ኮትዲቯር በ2021 በወዳጅነት ጨዋታ ቡርኪናፋሶን 2 ለ 1 ስታሸነፍ ነበር ያስቆጠረው። አማድ ዲያሎ ዘንድሮ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ድንቅ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል። አማድ በውድድሩ ላይ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች ሶስት ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን አንድ ለግብ የሚሆን ግብ አመቻችቶ አቀብሏል። ኮትዲቯር ከሞዛምቢክ፣ ካሜሮን እና ቡርኪናፋሶ ጋር ባደረገቻቸው ጨዋታዎች የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተምርጧል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቯር ሩብ ፍጻሜ እንድትደርስ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። ኮትዲቯር ከግብጽ በሩብ ፍጻሜው ነገ ከግብጽ ጋር ምሽት አራት ሰዓት ላይ በአጋዲር ስታዲየም የምታደርገው ጨዋታ በጉጉጉት ይጠበቃል። ሀገሩ በጠዋታው ላይ ከአማድ ብዙ ትጠብቃለች። ወደ ክለብ እንቅስቃሴው ስንመለስ አማድ በማንችስተር ዩናይትድ ስብስብ ውስጥ ቁልፍ የሚባል ተጫዋች ነው። ፈጣን ኳስን የማንከበላል ክህሎቱ፣ ፍጥነቱ ፣ የቴክኒክ አቅሙ፣ ጨዋታን የማንበብ ብቃቱ እና ሁለቱንም እግሩን የመጠቀም አቅሙ አልፎም ተጫዋቾችን በቄንጥ የሚያልፍበት መንገድ ተጫዋቹን እያስወደሰው ነው። አማድ ዲያሎ ከክንፍ ተጫዋችነቱ ባሻገር የአጥቂ አማካይ ሆኖ መጫወትም ይችላል። እ.አ.አ በ2020 የ18 ዓመት ልደቱን ተከትሎ ተጫዋቹ ስሙን ከአማድ ትራኦሬ ወደ አማድ ዲያሎ አስቀይሯል። አማድ ካለው ድንቅ ብቃት አንጻር ወደፊት በክለብ እና ብሄራዊ ቡድን ደረጃ ድንቅ ጊዜን ካሳለፉ ታዋቂ የአፍሪካ ተጫዋቾች ተርታ የመሰለፉ ጉዳይ አያጠራጥርም።
በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ብዙ ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን ያቀበሉ ተጫዋቾች
Jan 5, 2026 208
በእግር ኳስ ጨዋታ ከግብ አስቆጣሪዎች ጀርባ ኳስን ፍትፍት አርገው ጨርሰው የሚያቀብሉ ተጫዋቾች አሉ። አንድ ተጫዋች ግብ ሲያገባ ከማግባቱ ባልተናነሰ ማን ኳሱን አቀበለው? የሚለው ጥያቄ በተመልካቾች ይነሳል። በእግር ኳስ እድገት ውስጥ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለጎል ኳስ አመቻችተው የሚያቀብሉ ተጫዋቾች ትልቅ ዋጋ ይሰጣቸዋል። ማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪምን አሰናበተ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች እየተካሄዱ ይገኛሉ። የ33 ዓመቱ የሴኔጋል አምበል ሳዲዮ ማኔ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ካስቆጠረው አንድ ግብ በተጨማሪ ሶስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል የቀዳሚነቱን ስፍራ ይዟል። ማኔ ሴኔጋል ለሩብ ፍጻሜ እንድታልፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ ትልቅ የሚባል ነው። ስምንት ተጫዋቾች በተመሳሳይ ሁለት ለግብ የሚሆኑ ግቦችን አመቻችተው አቀብለዋል። ናይጄሪያውያኑ አዴሞላ ሉክማን እና አሌክስ ኢዎቢ፣ የሞሮኮው አዝዲን ኡናሂ፣ የአልጄሪያው አኒስ ሃጂ-ሙሳ፣ የቡርኪናፋሶው ዳንጎ ኡታራ፣ የቱኒዚያው ሃኒባል ሜጅብሪ፣ የደቡብ አፍሪካው ላይል ፎስተር እና የታንዛንያ ኖቫቱስ ሞሮሺ በሁለት ግቦች ላይ እጃቸው ያለበት ተጫዋቾች ናቸው። የናይጄሪያው የክንፍ የመስመር ተጫዋች አዴሞላ ሉክማን ሁለት ግቦችን በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አስቆጥሯል። የኮትዲቯሩ ክርስቶፈር ኦፔሪ እና የናይጄሪያው ሳሙኤል ቹኩዌዜ በተመሳሳይ አንድ አንድ ግቦች ከመረብ ላይ እንዲቆጠሩ የቀጥታ ተሳትፎ አድርገዋል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬን (ካፍ) የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ኮከብ ተጫዋች ምርጫ ላይ ካስቀመጣቸው መመዘኛ መስፈርቶች አንዱ ማን ብዙ ለጎል የሚሆን አቀበለ? የሚለው ይገኝበታል። 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እስከ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የግብ አግቢዎችና የኳስ አቀባዮቹ ፉክክር በያዘው ግለት ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል።