አርእስተ ዜና
በሲዳማ ክልል ማረሚያ ቤቶች  ያለው የታራሚዎች  መልካም አያያዝ  ተጠናክሮ መቀጠል አለበት - ቋሚ ኮሚቴው
Jun 5, 2023 42
ሀዋሳ ግንቦት 28 /2015 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ማረሚያ ቤቶች በታራሚዎች አያያዝ ዙሪያ ያለውን መልካም ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው ዛሬ የሀዋሳ ማዕከላዊ ማረሚያ ተቋምንና በሀዋሳ ከተማ የመሀል ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያን ተመልክቷል። በዚህ ወቅት የቋሚ ኮሚቴው ቡድን መሪ ወይዘሮ ዘሀራ ቢፍቱ፤ በማረሚያ የሚገኙ ታራሚዎች ሰብዓዊ መብቶቻቸው ተከብሮላቸውና አስፈላጊ መሰረታዊ አቅርቦቶች እንደተሟሉላቸው ከምልከታቸው መረዳታቸውን ገልጸዋል። ለታራሚዎቹ የምግብ፣ የህክምና አገልግሎትና ትምህርት ከአንደኛ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እየተማሩ እንደሚገኙ፤ በማረሚያው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስዶ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባት የቻለ ታራሚ እንዳለ ማወቅ መቻላቸውን ጠቅሰዋል። በተለያዩ መስኮች በማህበር ተደራጅተው ስራ እንዲሰሩና ገቢ አግኝተው ከራሳቸው ባለፈ ቤተሰቦቻቸውን መደጎም የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩንም መረዳት እንደቻሉ ጠቁመዋል። በአጠቃላይ በማረሚያው ያለው የሰብዓዊ መብት አያያዝ መልካም ሁኔታ ለሌሎችም ተሞክሮ መሆን የሚችል እንደሆነ ገልጸው፤ ከማደሪያ ቤቶች አንጻር ጥበት መኖሩ እንደክፍተት የታየ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል። በማረሚያ ቤቱ ባየነው ነገር ተደስተናል፤ በቀጠሮ የሚመላለስ እንደሌለ ተረድተናል ያሉት ቡድን መሪዋ፤ ከይቅርታና ምህረት ጋር ተያይዞ ያለው ቅሬታ ለመፍታት ጥናት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የሲዳማ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ኮንታሞ ቡርቃ በበኩላቸው፤ ክልሉ ከተመሰረተ ሶስት ዓመት እድሜ እንዳለውና ከዕድሜው አንጻር ያሉት ሁለት ማረሚያ ቤቶች ብቻ በመሆናቸው የታራሚዎች ቁጥርና ማደሪያ ክፍል አለመጣጣም እንደሚታይ አስረድተዋል። በማረሚያ ቤቱ ከለውጡ በፊት በነበረው ሁኔታ በታራሚዎች ላይ በኮሚሽኑ ፖሊሶች ይደርስ የነበረ ሰብዓዊ መብት ጥሰትን ከታራሚዎችና ከፖሊስ ሀይሉ ጋር በመነጋገር ጥፋቶችን በመለየት እርምጃ በመወሰዱ ማስቀረት ተችላል ብለዋል። በማረሚያ ቤቱ ከሚገኙ የህግ ታራሚዎች ውስጥ አስተያየቱን የሰጠው የታራሚዎች ኮሚቴ ጸሀፊ አዳነ ለማ እንዳለው፤ ከለውጡ በፊት በታራሚዎች ላይ ይደርስ የነበረው በደልና የመብት ጥሰት ቀርቷል። አሁን ሁሉም ነገር ተለውጦ ታራሚው መብቱ ተከብሮለት በጥሩ ሁኔታ የእርማት ጊዜውን እንደሚያጠናቅቅም ገልጿል።  
ፅንፈኝነትንና አክራሪነትን በመከላከል ጠብቀን እና ተንከባክበን ያቆየነውን አንድነት እና ሰላምን ማጽናት ይገባናል- አቶ አብዱጀባር መሀመድ
Jun 5, 2023 38
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ ፅንፈኝነትንና አክራሪነትን በመከላከል ጠብቀን እና ተንከባክበን ያቆየነውን አንድነት እና ሠላማችንን ማጽናት ይገባናል ሲሉ በብልፅግና ፓርቲ ሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዱጀባር መሀመድ ተናገሩ። የሀረሪ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ በክልላዊና ሀገራዊ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል።   መድረኩ በክልሉ ሰላምን ለማጠናከር እና ለዘላቂ ልማትና ብልጽግና ለማረጋገጥ በጋራ መቆም እንደሚያስችል ገልጸዋል። ፅንፈኝነትንና አክራሪነትን በመከላከል ጠብቀን እና ተንከባክበን ያቆየነውን አንድነት እና ሠላማችንን ማጽናት እንደሚገባ ጠቁመው በዚህም አመራሩ የመሪነት ሚናውን በአግባብ እንዲወጣ አሳስበዋል። መላው የክልሉ ህዝብም እየታየ የሚገኘውን አንፃራዊ ሰላም እና አብሮነትን መጠበቅና መንከባከብ እንዳለበት አመላክተዋል። ከከፍተኛ አመራሮች በተጨማሪ በክልሉ ከሁሉም ቀበሌዎች የተውጣጡ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይቶች እየተካሄዱ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ውይይቱ ለሶስት ቀናት እንደሚቆይ ከክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በደቡብ ክልል የኮሌራ በሽታ ተጋላጭነትን ለመቀነስ ግንዛቤን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
Jun 5, 2023 43
ዲላ ግንቦት 28/2015 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ክልል የሚታየውን የኮሌራ በሽታ ስርጭትና ተጋላጭነት ለመቀነስ የኅብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ከመገናኛ ብዙሃን አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በበሽታው ስርጭት ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠርን ዓላማ ያደረገ የውይይት መድረክ ዛሬ በዲላ ከተማ አካሂዷል። በቢሮው የማህበረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ወንድዬ በሽር በመደረኩ እንዳሉት የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት በሽታውን በመከላከልና በመቆጣጠር ተግባር ሚናቸውን መወጣት አለባቸው። በተለይም በክልሉ በሚገኙ አንዳንድ ቦታዎች የታየውን ስርጭት ለመግታት ቢሮው ከሌሎች ባለድርሻ አካላትና ማህበረሰብ ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል። ባለፉት አምስት ቀናት በተካሄደ የክትባት ዘመቻ 178 ሺህ በላይ ዜጎች መከተባቸውንና ሌሎች የጤና አገልግሎት ተደራሽ እየተደረጉ መሆናቸውን ከፍተኛ ባለሙያው አስረድተዋል። በክልሉ የበሽታው ምልክቶች ከታየባቸው 2 ሺህ 511 ዜጎች ውስጥ ከ93 በመቶ የሚልቁት የሕክምና አገልግሎት አግኝተው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ተናግረዋል። ለበሽታው ያለውን ተጋላጭነት ለመግታት የህብረተሰቡን የንጽህና አጠባበቅ ግንዛቤ ለማሳደግ የጋራ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አቶ ወንድዬ አስገንዝበዋል። የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ህብረተሰቡ የራሱንና የአካባቢውን ንጽህና እንዲጠብቅ በማስተማር ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል። ''የበሽታውን ስርጭት ለመግታት የተቀናጀ ምላሽ ያስፈልጋል'' ያሉት ደግሞ የክልሉ ጤና ቢሮ የኮሙኒኬሽን ሃላፊ አቶ ቀዲሬላ አህመድ ናቸው።   በተለይ ለህብረተሰቡ የንጹህ ውሃ ተደራሽነትን ከማሳደግ ባለፈ፤ በሽታውን በዘላቂነት እንዲከላከል ግንዛቤውን ማሳደግ ይገባል ብለዋል። በክልሉ የክረምት ወቅትን ተከትሎ ለወረርሽኙ ምቹ ሁኔታ እንዳይፈጠር የጥንቃቄ ሥራዎች እንዲከናወኑም ጠቁመዋል። በተለይ የተበከለ ፈሳሽና ደረቅ ቆሻሻ ለበሽታው መስፋፋት ምክንያት ስለሚሆኑ ህብረተሰቡ ለግልና አካባቢ ጽዳት አጠባበቅ ትኩረት እንዲሰጥ በተቀናጀ መንገድ ትምህርት እየተሰጠ ነው ብለዋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ሥራ አስኪያጅ መምህር አስናቀ እንድሪያስ መድረኩ በበሽታው ስርጭት ዙሪያ ወቅታዊ መረጃ የሰጠ፣ በሽታውን ስርጭት ለመግታት የመገናኛ ብዙሃን ሚና ያመላከተ መሆኑን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ በሚረዳው መልኩ በማስተማር ከበሽታው እንዲጠበቁ ሙያዊ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።  
በኢትዮጵያ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ የቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል ተገኘ
Jun 5, 2023 55
አርባ ምንጭ ግንቦት 28/2015 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ የቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል መገኘቱን አንድ ዓለም አቀፍ የተመራማሪ ቡድን አስታወቀ። 12 አባላትን የያዘው ዓለም አቀፍ የቅሪተ አካል ተመራማሪ ቡድን በባሌ ተራሮች ስር ባካሄደው ተከታታይ አምስት ዓመታትን በፈጀ ጥናት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዕድሜ ያስቆጠረ የቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል ማግኘቱን ገልጿል። በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የታሪክና ቅርስ ጥናት ትምህርት ክፍል አዘጋጅነት በተገኘው ቅሪተ አካልና የጥናት ሂደቱን የተመለከተ ለተለያዩ አካላት ገለጻ ተደርጓል። በውይይቱ ላይ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና በእሥራኤል አገር ሂብሪው ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም ቅሪተ አካሉን ያገኘው ተመራማሪዎች ቡድን አስተባባሪ ዶክተር ተገኑ ጎሳ ጥናቱንና ግኝቱን የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚህም ቡድኑ በባሌ ሰንሰለታማ ተራሮች ግርጌ ስር ባደረገው ጥናት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዕድሜ ያለው የቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል መገኘቱን አረጋግጠዋል። ቅሪተ አካሉ የተገኘው በፈረንጆች አቆጣጠር በ2017 ዓ.ም ሲሆን የግኝቱ ትክክለኝነት የበለጠ ለማጠናከር ተጓዳኝ የጥናት ሂደቶች ሲከናወኑ ቆይተው ግኝቱ ይፋ ሆኗል ብለዋል። በጥናቱ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ ያለው የቀይ ቀበሮ ግማሽ የመንጋጋው ክፍል የተገኘ መሆኑን አረጋግጠው እስከ ቅርብ ጊዜ የተለያዩ ጥናቶች ሲደረግበት መቆየቱን ገልጸዋል። ይህም ይበልጥ ጥናቱ ጎልብቶ የተረጋገጠ መረጃ ለዓለም ለማበርከት ሲባል መሆኑን ገልጸው ሂደቶቹ መጠናቀቃቸውን ተከትሎ ዛሬ ይፋ መደረጉን ነው የተናገሩት። በዚሁም ቅሪተ አካሉ አሁን ካሉ የቀይ ቀበሮዎችና መሰል እንስሳት ጋር ያለው አንድነትና ልዩነት እንዲሁም የዕድሜና ሌሎች ጥናቶች መደረጋቸውን አስረድተዋል። ቀይ ቀበሮዎቹ በሀገራችን በሰሜንና ባሌ ተራሮች አካባቢ የሚገኙ ሲሆን ህብረተሰቡ ለግጦሽና ለእርሻ መሬት ፍለጋ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ብሎም ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተዳምሮ የዱር አራዊቱ በአሁኑ ሰዓት የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበት መሆኑን አስገንዝበዋል።   የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዝዳንት ተባባሪ ፕሮፈሰር በሃይሉ መርደኪዮስ፣ ግኝቱ ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ በሌሎች ዓለማት የማይገኙ የዱር እንስሳት ባለቤት መሆኗን ለማረጋገጥ ተጨማሪ አቅም የሚሆን ማስረጃ መሆኑን ገልጸዋል። የመርሃ ግብሩ ዓላማም በመጥፋት ላይ ያለውና ብቸኛ የሆነው ቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል መገኘቱን ለህዝብ ይፋ ለማድረግ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመሆኑም መንግስትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት ዝሪያውን ከመጥፋት መታደግ እንዳለበትም ጠቁመዋል። ይህ ግኝት በኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች አስተባባሪነት የተገኘ መሆኑን ያስታወሱት ደግሞ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባህልና ቋንቋ ጥናት ተቋም ዳይሬክተር ዶክተር ሰይድ አህመድ ናቸው። በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ብርቅዬ እንስሳት ለቱሪዝም ክፍለ ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ጠቅሰው ለዝሪያቸው አስፈላጊው ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባም አመልክተዋል። በዚህ ረገድ ዩኒቨርሲቲው እንደ ከፍተኛ ተቋም በጥናት የተደገፈ መረጃ በመስጠት የማንቃትና ሌሎች ሃላፊነቶች እየተወጣ መሆኑንም አብራርተዋል። ጥናቱ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ2013 እስከ 2017 ዓ.ም ተከታታይ ዓመታት የፈጀ ሲሆን በዚሁም ሁለት ኢትዮጵያዊያን ጨምሮ 10 የተለያዩ ሀገራት ተመራማሪዎች በአጠቃላይ 12 ዓለም አቀፍ ተመራማሪዎች መሳተፋቸው ተመላክቷል፡፡    
የሚታይ
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሀብት ብክነትን ለመቀነስና የአሰራር ሥርዓት ለማሻሻል ጥረት እየተደረገ ነው-  የዩኒቨርሲቲው  ከፍተኛ አመራሮች
Jun 5, 2023 47
  ዲላ ግንቦት 28/2015 (ኢዜአ) --የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሃብት ብክነትንና ለመቀነስና የአሰራር ሥርዓትን በማሻሻል ብልሽቶችን ለማረም እየሰራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ፡፡ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ዩኒቨርሲቲውን በቀጣይ የራስ ገዝ ለማድረግ ምቹ መደላድል የሚፈጥሩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውንም ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ፍቃዱ ወልደማሪያም እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው በኦዲት ግኝት የተለዩና ሌሎች ችግሮችን ለማስተካከል እየተሰራ ነው። በዚህም ብልሽቶችን በማረም አመራሩን ሪፎርም ከማድረግና ተጠያቂነትን ከማስፈን ጀምሮ የአሰራር ሥርዓቱን እስከ ማሻሻል የዘለቁ ተግባራት እየተካሄዱ ነው ብለዋል። በሁሉም የትምህርት ክፍሎች የሚታዩ ድክመቶችንና ጥንካሬዎችን በጥናት በመለየት የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑንም ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል። በተለይም ብልሽቶች ገነው በወጡባቸው በግንባታ ፕሮጀክቶችና በተማሪዎች አገልግሎት የሚታዩ ችግሮችን በመለየት የሕግ ተጠያቂነትን የማረጋገጥና የተመዘበረ ሃብት የማስመለስ ሥራዎች እየተካሄዱ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለተቋም ግንባታ የሰው ኃይል ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፣ በሰው ሃብት አስተዳደርና ልማት ላይ የታዩ ብልሽቶች እስኪታረሙ በጊዜያዊነት ቅጥርና ምደባ እንዲቆም መወሰኑን አስታውቀዋል።   በዩኒቨርሲቲው እየተከናወኑ ያሉ የለውጥ ሥራዎች ብልሽቶችን በማረም ለኦዲት ግኝት ምላሽ ከመስጠት ባለፈም፤ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ ለማድረግ የጸደቀውን ዓዋጅ ለመተግበር አቅም እንደፈጠረ አመላክተዋል። በተለይ የሃብት ብክነትን ለመቀነስና የአሰራር ሥርዓት በማሻሻል ክፍተቶችን በዘላቂነት ለማረም እየተሰራ መሆኑን ዶክተር ፍቃዱ ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተከናወኑት የዳታ ማዕከል፣ የመምህራን መኖሪያ ቤቶችና መሰል የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ የግዥ ብቻ ሳይሆን፣ የፕሮጀክት አስተዳደር ችግር እንዳለባቸው ያነሱት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የቢዝነስና ተቋማዊ ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ዳራሪ ሰናይ ናቸው። የዘገዩ፣ የግንባታ ውልና የመረካከቢያ ሰነድ የሌላቸው በሚል ፕሮጀክቶችን በስድስት ዘርፎች በመከፋፈል በተቋም አቅምና በባለድርሻ አካላት የማጥራት ሥራ መከናወኑን አስረድተዋል።   በዚህም የመንግሥትን የግዥና ንብረት አስተዳደር ዓዋጅን ባልተከተሉና ችግር ያለባቸው የግንባታና አማካሪዎች ጋር የነበሩ ውሎች ሙሉ በሙሉ እንዲቆሙ መደረጉን አስታውቀዋል። በተለይ የተጋነኑ የግዥ ውሎችን በመሰረዝና አማካሪ ድርጅቶችን በማገድ የመንግሥትና የዩኒቨርሲቲውን ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ ለህጋዊ ተቋራጮች መተላለፋቸውን ምክትል ፕሬዚዳንቱ አብራርተዋል፡፡ በዚህም የዘገዩ የመምህራን ቤቶች ግንባታና መለስተኛ ስታዲዬም ግንባታቸው ተጠናቅቆ ለአገልግሎት መብቃታቸውን ገልጸዋል። የዩኒቨርሲቲውን አሰራር ችግሮች በማረም ቁመናውን ከማስተካከል በላይ የራስ ገዝ አስተዳደርን እውን የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል። በተለይ የፋይናንስ ነጻነትን ለማረጋገጥ ዓዋጁን መሠረት ያደረጉ የገቢ አቅም ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ኢንጂነር ዳራሪ አስታውቀዋል። በዩኒቨርሲቲው በኦዲት ግኝት የተለየ ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብና ለሌሎች ብልሹ አሰራሮች እንዲስተካከሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅጣጫ ማስቀመጡ የሚታወስ ነው።    
ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፍትሕ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ
Jun 5, 2023 44
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ) ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፍትሕ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በወጡ ሕጎችና ማሻሻያዎች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ። የፍትሕ ሚኒስቴር አገራዊ ለውጡን ተከትሎ የወጡ የሕግና አሠራር ማሻሻያዎችን በሚመለከት ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የፍትሕ ቢሮ፣ የፍርድ ቤቶች የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል፡፡ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣ የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት፣ የጠበቆች እና መሰል ሕጎች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ቀርቧል፡፡ የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ዓለምአንተ አግደው፤ ለውጡን ተከትሎ በፍትሕና ሌሎችም ተቋማት የማሻሻያ ሥራዎች በስፋት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም አዲስ የወጡ አዋጆችና ማሻሻያዎችን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በአግባቡ መተግበር እንዲያስችለው የግንዛቤ መድረኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። የጊዜያዊ አስተዳደሩ የፍትሕ ተቋማት በለውጡ ዓመታት በወጡ አዋጆች ላይ ሙሉ መረዳት ኖሯቸው ክልሉን በመደበኛ ሕግ ማስተዳደር እንዲችሉ የግንዛቤ መድረኩ ወሳኝ መሆኑንም ጠቁመዋል። ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎችና የዘርፉ ተዋንያን ጋር የሚደረገው ውይይት የፍትሕ ሥርዓቱን ለማሳለጥ ያግዛል ብለዋል፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ሀዱሽ ተስፋ፤ መድረኩ በመንግሥት የተደረጉ የፍትሕ ማሻሻያዎችን በአግባቡ በመረዳት ተግባራዊ ለማድረግ አጋዥ መሆኑን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ይበልጥ እንዲጠናከር የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ  
Jun 5, 2023 67
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ይበልጥ እንዲጠናከር ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተጠቆመ። በኢትዮጵያ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች " የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ እና አንዳንድ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች " በሚል ርዕስ ውይይት አድርገዋል፡፡   በመድረኩ የውይይት የመነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት የፌዴራሊዝም እና መልካም አስተዳደር ምሁሩ ዶክተር ዘመላክ አይተነው፤ የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት የመድብለ ፓርቲ ስርዓት እንዲኖር የሚያስችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን አንስተው ይህም ለተጠናከረ መድብለ ፓርቲ ግንባታ ሕጋዊ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። በተጨማሪም የተለያዩ አገር አቀፍ እና ክልል አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖራቸው እና ሕገ-መንግስቱ ለቡድንና ግለሰብ መብቶች እውቅና መስጠቱ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ለመገንባት በጎ ሚና እንዳላቸው አመልክተዋል። ነገር ግን ጠንካራና የተደራጁ ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለመኖራቸው የመድብለ ፓርቲ ስርዓት በሚፈለገው አግባብ እንዳይጎለብት አድርጓል ነው ያሉት ዶክተር ዘመላክ። በመሆኑም የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ለማጎልበት የተጀመሩ ስራዎች ይበልጥ ሊጠናከሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ የቦርዱ አዋጅም ሆነ ሕገ-መንግስቱ የመድብለ ፓርቲ አካሄድን የሚፈቅድ ነው ብለዋል፡፡ በዚሁ መሰረት 21 አገራዊ እና 41 ክልላዊ በድምሩ 62 የፖለቲካ ፓርቲዎች በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ሰብሳቢው አክለው የመድብለ ፓርቲው ስርዓት ይበልጥ እንዲጎለበት ሁሉም ፓርቲዎች ለሕግ ተገዢ መሆን እንዳለባቸው አመልክተዋል። በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ማጎልበት ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ኃላፊነት አለመሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ሚና መወጣት አለበት ነው ያሉት፡፡   የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ አመራር ዮሐንስ ተሰማ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ የፓለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት የተከናወኑ ስራዎች ለመድብለ ፓርቲ ስርዓት ትግበራ ምቹ ሁኔታ የፈጠሩ መሆናቸውን አመልክተዋል። ለአብነትም ተፎካካሪ ፓርቲዎች በመንግስት የአመራርነት መዋቅር ውስጥ መካተታቸውን አንስተዋል።   የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ዶክተር መብራቱ ዓለሙ በበኩላቸው የተጀመረው የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት በቀጣይ ለሚካሄደው አገራዊ የምክክር ሂደት መሳካት ሚናው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል። የፖለቲካ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤትም በውይይቶቹ የሚነሱ ሃሳቦችን አደራጅተው ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን እንደሚሰጡ ጠቁመዋል። ዛሬ የተጀመረው የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት መድረክ በቀጣይም በሌሎች አጀንዳዎች የሚቀጥል መሆኑ ተጠቁሟል።  
ኢትዮጵያ እና ብራዚል ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ተስማሙ
Jun 5, 2023 93
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ብራዚል ያላቸውን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ተስማምተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ ጋር የሁለቱን አገራት ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙርያ ዛሬ መክረዋል። አቶ ደመቀ መኮንን ኢትዮጵያ ከብራዚል ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ጊዜው አሁን መሆኑን የገለፁ ሲሆን ፤ ኢትዮጵያ በብራዚል ዳግም ኤምባሲዋን መክፈቷም ግንኙነቱን ይበልጥ ከፍ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ አስታውሰዋል። ብራዚል በኢትዮጵያ በዘላቂ የደን ልማት አስተዳደር በጥጥ ምርት እና በአፈር ጥበቃ ላይ ለኢትዮጵያ እያደረገች ላለቸው መልካም አበርክቶም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አድናቆታቸውን ገልፀዋል። አቶ ደመቀ ኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት፣ አቪዬሽን፣ ቱሪዝም፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ በአከባቢ ጥበቃ፣ በማዕድን እና ኢነርጂ ዘርፎች ከብራዚል ጋር በትብብር ለመሥራት ያላትን ፍላጎት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አረጋግጠውላቸዋል። የብራዚሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ በበኩላቸው፣ አገራቸው በስፖርት እና የተለያዩ መስኮች ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ጠቅሰው ፤ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባሻገር በባለ ብዙ ወገን የዲፕሎማሲ መድረኮች ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። በሁለቱ ሃገራት መካከል ቀጣይ የፖለቲካ ውይይት እንዲካሄድም መግባባት ላይ መደረሱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።          
ማስታወቂያ
ፖለቲካ
ፅንፈኝነትንና አክራሪነትን በመከላከል ጠብቀን እና ተንከባክበን ያቆየነውን አንድነት እና ሰላምን ማጽናት ይገባናል- አቶ አብዱጀባር መሀመድ
Jun 5, 2023 38
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ ፅንፈኝነትንና አክራሪነትን በመከላከል ጠብቀን እና ተንከባክበን ያቆየነውን አንድነት እና ሠላማችንን ማጽናት ይገባናል ሲሉ በብልፅግና ፓርቲ ሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዱጀባር መሀመድ ተናገሩ። የሀረሪ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ በክልላዊና ሀገራዊ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል።   መድረኩ በክልሉ ሰላምን ለማጠናከር እና ለዘላቂ ልማትና ብልጽግና ለማረጋገጥ በጋራ መቆም እንደሚያስችል ገልጸዋል። ፅንፈኝነትንና አክራሪነትን በመከላከል ጠብቀን እና ተንከባክበን ያቆየነውን አንድነት እና ሠላማችንን ማጽናት እንደሚገባ ጠቁመው በዚህም አመራሩ የመሪነት ሚናውን በአግባብ እንዲወጣ አሳስበዋል። መላው የክልሉ ህዝብም እየታየ የሚገኘውን አንፃራዊ ሰላም እና አብሮነትን መጠበቅና መንከባከብ እንዳለበት አመላክተዋል። ከከፍተኛ አመራሮች በተጨማሪ በክልሉ ከሁሉም ቀበሌዎች የተውጣጡ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይቶች እየተካሄዱ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ውይይቱ ለሶስት ቀናት እንደሚቆይ ከክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ይበልጥ እንዲጠናከር የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ  
Jun 5, 2023 67
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ይበልጥ እንዲጠናከር ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተጠቆመ። በኢትዮጵያ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች " የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ እና አንዳንድ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች " በሚል ርዕስ ውይይት አድርገዋል፡፡   በመድረኩ የውይይት የመነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት የፌዴራሊዝም እና መልካም አስተዳደር ምሁሩ ዶክተር ዘመላክ አይተነው፤ የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት የመድብለ ፓርቲ ስርዓት እንዲኖር የሚያስችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን አንስተው ይህም ለተጠናከረ መድብለ ፓርቲ ግንባታ ሕጋዊ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። በተጨማሪም የተለያዩ አገር አቀፍ እና ክልል አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖራቸው እና ሕገ-መንግስቱ ለቡድንና ግለሰብ መብቶች እውቅና መስጠቱ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ለመገንባት በጎ ሚና እንዳላቸው አመልክተዋል። ነገር ግን ጠንካራና የተደራጁ ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለመኖራቸው የመድብለ ፓርቲ ስርዓት በሚፈለገው አግባብ እንዳይጎለብት አድርጓል ነው ያሉት ዶክተር ዘመላክ። በመሆኑም የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ለማጎልበት የተጀመሩ ስራዎች ይበልጥ ሊጠናከሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ የቦርዱ አዋጅም ሆነ ሕገ-መንግስቱ የመድብለ ፓርቲ አካሄድን የሚፈቅድ ነው ብለዋል፡፡ በዚሁ መሰረት 21 አገራዊ እና 41 ክልላዊ በድምሩ 62 የፖለቲካ ፓርቲዎች በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ሰብሳቢው አክለው የመድብለ ፓርቲው ስርዓት ይበልጥ እንዲጎለበት ሁሉም ፓርቲዎች ለሕግ ተገዢ መሆን እንዳለባቸው አመልክተዋል። በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ማጎልበት ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ኃላፊነት አለመሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ሚና መወጣት አለበት ነው ያሉት፡፡   የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ አመራር ዮሐንስ ተሰማ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ የፓለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት የተከናወኑ ስራዎች ለመድብለ ፓርቲ ስርዓት ትግበራ ምቹ ሁኔታ የፈጠሩ መሆናቸውን አመልክተዋል። ለአብነትም ተፎካካሪ ፓርቲዎች በመንግስት የአመራርነት መዋቅር ውስጥ መካተታቸውን አንስተዋል።   የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ዶክተር መብራቱ ዓለሙ በበኩላቸው የተጀመረው የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት በቀጣይ ለሚካሄደው አገራዊ የምክክር ሂደት መሳካት ሚናው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል። የፖለቲካ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤትም በውይይቶቹ የሚነሱ ሃሳቦችን አደራጅተው ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን እንደሚሰጡ ጠቁመዋል። ዛሬ የተጀመረው የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት መድረክ በቀጣይም በሌሎች አጀንዳዎች የሚቀጥል መሆኑ ተጠቁሟል።  
ኢትዮጵያ እና ብራዚል ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ተስማሙ
Jun 5, 2023 93
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ብራዚል ያላቸውን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ተስማምተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ ጋር የሁለቱን አገራት ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙርያ ዛሬ መክረዋል። አቶ ደመቀ መኮንን ኢትዮጵያ ከብራዚል ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ጊዜው አሁን መሆኑን የገለፁ ሲሆን ፤ ኢትዮጵያ በብራዚል ዳግም ኤምባሲዋን መክፈቷም ግንኙነቱን ይበልጥ ከፍ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ አስታውሰዋል። ብራዚል በኢትዮጵያ በዘላቂ የደን ልማት አስተዳደር በጥጥ ምርት እና በአፈር ጥበቃ ላይ ለኢትዮጵያ እያደረገች ላለቸው መልካም አበርክቶም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አድናቆታቸውን ገልፀዋል። አቶ ደመቀ ኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት፣ አቪዬሽን፣ ቱሪዝም፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ በአከባቢ ጥበቃ፣ በማዕድን እና ኢነርጂ ዘርፎች ከብራዚል ጋር በትብብር ለመሥራት ያላትን ፍላጎት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አረጋግጠውላቸዋል። የብራዚሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ በበኩላቸው፣ አገራቸው በስፖርት እና የተለያዩ መስኮች ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ጠቅሰው ፤ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባሻገር በባለ ብዙ ወገን የዲፕሎማሲ መድረኮች ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። በሁለቱ ሃገራት መካከል ቀጣይ የፖለቲካ ውይይት እንዲካሄድም መግባባት ላይ መደረሱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።          
በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በአዳዲስ መስኮች ማሳደግ ይገባል-አምባሳደር ሰይድ ሙሃመድ
Jun 5, 2023 70
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በአዳዲስ መስኮች ማሳደግ እንደሚገባ በኩዌት የኢትዮጵያ አምባሳደር ሰይድ ሙሃመድ ገለጹ። በኩዌት የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር በመሆን የተሾሙት አምባሳደር ሰይድ ሙሃመድ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኩዌት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ ሳሌም አብደላህ አል-ጀብር አል-ሳባህ አቅርበዋል። በዚህ ወቅት በነበራቸው ውይይትም በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በአዳዲስ መስኮች ማሳደግ ይገባል ሲሉ አምባሳደር ሰይድ ሙሃመድ ገልጸዋል። በኩዌት በሚኖራቸው ቆይታም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር አንደሚሰሩና ለዚህም የኩዌት መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ያላቸውን እምነት ጠቁመዋል።   የኩዌት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ ሳሌም አብደላህ አል-ጀብር አል-ሳባህ በበኩላቸው ኩዌት ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽና ባለ-ብዙ ወገን ግንኙነት አጠናክራ እንደምትቀጥል አሰታውቀዋል። አምባሳደር ሰይድ በኩዌት በሚኖራቸው ቆይታ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ለሚሰሩት ስራ ድጋፍ እንደሚያደርጉም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል። አምባሳደሩ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተላከ መልዕክት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማቅረባቸውን ከኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በስርአት አልበኞች ላይ እየተወሰደ ያለው የህግ ማስከበር እርምጃ ከግብ እንዲደርስ ህዝቡ ትብብር ማድረግ አለበት--አፈ ጉባኤ ፋንታይቱ ካሴ 
Jun 4, 2023 116
ሰቆጣ ግንቦት 27/2015 (ኢዜአ) መንግስት በስርአት አልበኞች ላይ እየወሰደ ያለው ህግ የማስከበር እርምጃ ከዳር እንዲደርስ ህዝቡ አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ አለበት ሲሉ የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ገለጹ። የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ በሰቆጣ ከተማ ተካሂዷል። የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታይቱ ካሴ በጉባኤው ላይ እንደገለጹት፣ አገራዊ ሰላምን በማረጋገጥ የተጀመረውን ለውጥ ዳር ለማድረስ ሁሉም ለሰላም ትኩረት ሰጥቶ መረባረብ አለበት። ለውጡን የማይፈልጉ አንዳንድ ሃይሎች ሃሳብን በምክክር ማሸነፍ ሲያዳግታቸው እየሄዱበት ያለው ፓለቲካ ተቀባይነት የለውም፤ ህዝብንም ለከፋ ችግር ያጋልጣል ብለዋል። መንግስት በስርአት አልበኝነት የሚንቀሳቀሱትን አካላት ስርዓት ለማስያዝ እየወሰደ ላለው ህግ የማስከበር እርምጃ የብሔረሰብ አስተዳደሩ ምክር ቤቱ ድጋፍ እንደማይለየው ገልጸዋል። የህግ ማስከበር እርምጃው ግቡን እንዲመታም ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ እንዳለበትም አፈ ጉባኤዋ አስገንዝበዋል። በዞኑ በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የነበሩ ወገኖች በተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት ወደቄያቸው መመለሳቸውን የገለጹት አፈ ጉባኤዋ፣ በአካባቢውም ሰላም እየሰፈነ መምጣቱን ተናግረዋል።   ወደቄያቸው ለተመለሱ ወገኖች ባሉበት የሰብዓዊ ድጋፎችን ለማድረግ የሚመለከታቸው ተቋማት አስቸኳይ የምግብ እህል ድጋፍ እንዲያደርጉም በምክር ቤቱ ስም ጠይቀዋል። የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ ህብረተሰቡ ወደመደበኛ ህይወቱ በመመለስ የአካባቢውን ኢኮኖሚ እንዲያነቃቃ በተሰራው ሥራ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው፣ በቀጣይም ይሄ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመለክተዋል። ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴዎች በኩል የአስፈፃሚ አካላትን ዕቅድ አፈጻጸም እንቅስቃሴ ለማወቅ በመስክ ምልከታ ጭምር እያደረገ ያለው ክትትልና ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታይቱ አመለክተዋል። በዞኑ እየተስተዋለ ባለው ሥራ አጥነት፣ የኑሮ ውድነት፣ ብልሹ አሰራርና ሌብነት ህዝቡ እየተማረረ በመሆኑ በቀጣይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል። ምክር ቤቱ ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው ጉባኤ የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸምንና የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን እቅድ ክንውን እንደሚገምግም ተመልክቷል።    
ህብረተሰቡ መደበኛ ህይወቱን ያለስጋት መምራት እንዲችል የጸጥታ አካላት ሃላፊነታቸውን በብቃት ሊወጡ ይገባል-- መምሪያው
Jun 4, 2023 123
ሆሳዕና ግንቦት 27/2015 (ኢዜአ) ፡-ህብረተሰቡ መደበኛ ህይወቱን ያለስጋት መምራት እንዲችል የጸጥታ አካላት ሙያዊ ስነምግባር ተላብሰው የተጣለባቸውን ሀላፊነት በተሻለ ብቃት ሊወጡ እንደሚገባ የሀድያ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ አስታወቀ። በሀድያ ዞን ፖሊስ መዋቅር ላይ የተስተዋሉ ጉድለቶችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ያተኮረ ዞን አቀፍ የአመራር ግምገማ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው። የሀድያ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ በእዚህ ወቅት እንዳሉት የጸጥታ አካላት የህዝብን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅና የማስጠበቅ ሃላፊነት አለባቸው።   በመሆኑም ህብረተሰቡ መደበኛ ህይወቱን ያለስጋት መምራት እንዲችል የጸጥታ አካላት ሙያዊ ስነምግባር በመላበስ ሃላፊነታቸውን በተሻለ ብቃት ሊወጡ ይገባል ብለዋል። ስነምግባርን ተላብሶ አገልግሎት በመስጠት በኩል በዞኑ ባሉ የጸጥታ መዋቅሮች የተስተዋሉ መጠነኛ ችግሮች እንዳሉ ገልጸው፣ ዞኑ ችግሮችን ለይቶ ለማረም እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የግምገማ መድረኩም የዜጎችን ደህንነትና ሰላም በማስጠበቅ ተግባር በተለይ በአንዳንድ የጸጥታ አካላት ላይ የሚስተዋለውን ችግር ለመፍታት ያለመ መሆኑን አስረድተዋል። ለሦስት ቀናት በሚቆየው የግምገማ መድረክ በተለይም በሆሳዕና ከተማና በሌሎች አካባቢዎች ከንጥቂያ፣ ዝርፊያና መሰል እየተበራከቱ ያሉ ወንጀሎችን ለማስቀረት የሚያስችል የጋራ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም አቶ ሳሙኤል ተናግረዋል። ከእዚህ በተጨማሪ ሃላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡትን በመለየት አስፈላጊ እርምጃ እንደሚወሰድና ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም ገልጸዋል። የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ዋና ሳጅን ተሾመ ባቲሶ በበኩላቸው፣ የዞኑ የፖሊስ መዋቅሮች በወንጀል ቅድመ መከላከልና ፍትሀዊ አገልግሎት በመስጠት በኩል ውስንነት እንዳለባቸው ገልጸዋል። "ከህዝብና ከመንግስት የተሰጠን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት ሲገባ ኃላፊነትን ወደጎን በመተው የግል ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ የሚሰሩ የፖሊስ አባላት ስለመኖራቸው በተለያየ መንገድ ለማወቅ ተችሏል" ብለዋል። ባልተገባ ተግባር በመሳተፍ ላይ የሚገኙ አባላትን በመለየት ተገቢ የሆነ እርምትና እርምጃ ለመውሰድ የግምገማ ውጤት እየተጠበቀ መሆኑንም ጠቁመዋል።   በዞኑ ፖሊስ መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ሳህሉ ኃይሌ በበኩላቸው እንዳሉት፣ ፖሊስ የአካባቢንና የማህበረሰቡን ሰላም የማስጠበቅ ሀገራዊ ኃላፊነት ተሰጥቶታል። ይሁንና ፖሊሳዊ ስነ ምግባርንና መርህን ተከትሎ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ በኩል ውስንነት እንዳለበት ተናግረዋል። "የማህብረሰቡን ሰላም አጠናክሮ የማስጠበቅ ሃላፊነቱን በአግባቡ በመወጣት በኩል ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የመድረኩ አስፈላጊነት ከፍተኛ ነው" ብለዋል። የፀጥታ አካላት ሙያዊ ስነ ምግባር በመላበስና ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ለአካባቢ ስጋት የሆኑ የጸጥታ ችግሮችን ለማስቀረት መስራት እንዳለባቸው የተናገሩት ደግሞ በመምሪያው የስታፍ ዲቪዥን ኃላፊው ኢንስፔክተር አብርሃም ቀጭኔ ናቸው። እንደእሳቸው ገለጻ፣ ማህበረሰብን ያሳተፈ የወንጀል መከላከል ተግባር የማህበረሰቡን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማስቀጠል ጠቀሜታው የጎላ ነው። በመድረኩ በዞኑ ከሚገኙ ከሁሉም የገጠር ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች የሰላምና ፀጥታና እንዲሁም የፖሊስ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው።  
ፖለቲካ
ፅንፈኝነትንና አክራሪነትን በመከላከል ጠብቀን እና ተንከባክበን ያቆየነውን አንድነት እና ሰላምን ማጽናት ይገባናል- አቶ አብዱጀባር መሀመድ
Jun 5, 2023 38
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ ፅንፈኝነትንና አክራሪነትን በመከላከል ጠብቀን እና ተንከባክበን ያቆየነውን አንድነት እና ሠላማችንን ማጽናት ይገባናል ሲሉ በብልፅግና ፓርቲ ሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዱጀባር መሀመድ ተናገሩ። የሀረሪ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ በክልላዊና ሀገራዊ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል።   መድረኩ በክልሉ ሰላምን ለማጠናከር እና ለዘላቂ ልማትና ብልጽግና ለማረጋገጥ በጋራ መቆም እንደሚያስችል ገልጸዋል። ፅንፈኝነትንና አክራሪነትን በመከላከል ጠብቀን እና ተንከባክበን ያቆየነውን አንድነት እና ሠላማችንን ማጽናት እንደሚገባ ጠቁመው በዚህም አመራሩ የመሪነት ሚናውን በአግባብ እንዲወጣ አሳስበዋል። መላው የክልሉ ህዝብም እየታየ የሚገኘውን አንፃራዊ ሰላም እና አብሮነትን መጠበቅና መንከባከብ እንዳለበት አመላክተዋል። ከከፍተኛ አመራሮች በተጨማሪ በክልሉ ከሁሉም ቀበሌዎች የተውጣጡ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይቶች እየተካሄዱ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ውይይቱ ለሶስት ቀናት እንደሚቆይ ከክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ይበልጥ እንዲጠናከር የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ  
Jun 5, 2023 67
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ይበልጥ እንዲጠናከር ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተጠቆመ። በኢትዮጵያ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች " የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ እና አንዳንድ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች " በሚል ርዕስ ውይይት አድርገዋል፡፡   በመድረኩ የውይይት የመነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት የፌዴራሊዝም እና መልካም አስተዳደር ምሁሩ ዶክተር ዘመላክ አይተነው፤ የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት የመድብለ ፓርቲ ስርዓት እንዲኖር የሚያስችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን አንስተው ይህም ለተጠናከረ መድብለ ፓርቲ ግንባታ ሕጋዊ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። በተጨማሪም የተለያዩ አገር አቀፍ እና ክልል አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖራቸው እና ሕገ-መንግስቱ ለቡድንና ግለሰብ መብቶች እውቅና መስጠቱ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ለመገንባት በጎ ሚና እንዳላቸው አመልክተዋል። ነገር ግን ጠንካራና የተደራጁ ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለመኖራቸው የመድብለ ፓርቲ ስርዓት በሚፈለገው አግባብ እንዳይጎለብት አድርጓል ነው ያሉት ዶክተር ዘመላክ። በመሆኑም የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ለማጎልበት የተጀመሩ ስራዎች ይበልጥ ሊጠናከሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ የቦርዱ አዋጅም ሆነ ሕገ-መንግስቱ የመድብለ ፓርቲ አካሄድን የሚፈቅድ ነው ብለዋል፡፡ በዚሁ መሰረት 21 አገራዊ እና 41 ክልላዊ በድምሩ 62 የፖለቲካ ፓርቲዎች በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ሰብሳቢው አክለው የመድብለ ፓርቲው ስርዓት ይበልጥ እንዲጎለበት ሁሉም ፓርቲዎች ለሕግ ተገዢ መሆን እንዳለባቸው አመልክተዋል። በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ማጎልበት ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ኃላፊነት አለመሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ሚና መወጣት አለበት ነው ያሉት፡፡   የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ አመራር ዮሐንስ ተሰማ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ የፓለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት የተከናወኑ ስራዎች ለመድብለ ፓርቲ ስርዓት ትግበራ ምቹ ሁኔታ የፈጠሩ መሆናቸውን አመልክተዋል። ለአብነትም ተፎካካሪ ፓርቲዎች በመንግስት የአመራርነት መዋቅር ውስጥ መካተታቸውን አንስተዋል።   የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ዶክተር መብራቱ ዓለሙ በበኩላቸው የተጀመረው የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት በቀጣይ ለሚካሄደው አገራዊ የምክክር ሂደት መሳካት ሚናው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል። የፖለቲካ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤትም በውይይቶቹ የሚነሱ ሃሳቦችን አደራጅተው ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን እንደሚሰጡ ጠቁመዋል። ዛሬ የተጀመረው የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት መድረክ በቀጣይም በሌሎች አጀንዳዎች የሚቀጥል መሆኑ ተጠቁሟል።  
ኢትዮጵያ እና ብራዚል ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ተስማሙ
Jun 5, 2023 93
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ብራዚል ያላቸውን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ተስማምተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ ጋር የሁለቱን አገራት ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙርያ ዛሬ መክረዋል። አቶ ደመቀ መኮንን ኢትዮጵያ ከብራዚል ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ጊዜው አሁን መሆኑን የገለፁ ሲሆን ፤ ኢትዮጵያ በብራዚል ዳግም ኤምባሲዋን መክፈቷም ግንኙነቱን ይበልጥ ከፍ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ አስታውሰዋል። ብራዚል በኢትዮጵያ በዘላቂ የደን ልማት አስተዳደር በጥጥ ምርት እና በአፈር ጥበቃ ላይ ለኢትዮጵያ እያደረገች ላለቸው መልካም አበርክቶም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አድናቆታቸውን ገልፀዋል። አቶ ደመቀ ኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት፣ አቪዬሽን፣ ቱሪዝም፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ በአከባቢ ጥበቃ፣ በማዕድን እና ኢነርጂ ዘርፎች ከብራዚል ጋር በትብብር ለመሥራት ያላትን ፍላጎት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አረጋግጠውላቸዋል። የብራዚሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ በበኩላቸው፣ አገራቸው በስፖርት እና የተለያዩ መስኮች ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ጠቅሰው ፤ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባሻገር በባለ ብዙ ወገን የዲፕሎማሲ መድረኮች ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። በሁለቱ ሃገራት መካከል ቀጣይ የፖለቲካ ውይይት እንዲካሄድም መግባባት ላይ መደረሱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።          
በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በአዳዲስ መስኮች ማሳደግ ይገባል-አምባሳደር ሰይድ ሙሃመድ
Jun 5, 2023 70
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በአዳዲስ መስኮች ማሳደግ እንደሚገባ በኩዌት የኢትዮጵያ አምባሳደር ሰይድ ሙሃመድ ገለጹ። በኩዌት የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር በመሆን የተሾሙት አምባሳደር ሰይድ ሙሃመድ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኩዌት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ ሳሌም አብደላህ አል-ጀብር አል-ሳባህ አቅርበዋል። በዚህ ወቅት በነበራቸው ውይይትም በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በአዳዲስ መስኮች ማሳደግ ይገባል ሲሉ አምባሳደር ሰይድ ሙሃመድ ገልጸዋል። በኩዌት በሚኖራቸው ቆይታም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር አንደሚሰሩና ለዚህም የኩዌት መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ያላቸውን እምነት ጠቁመዋል።   የኩዌት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ ሳሌም አብደላህ አል-ጀብር አል-ሳባህ በበኩላቸው ኩዌት ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽና ባለ-ብዙ ወገን ግንኙነት አጠናክራ እንደምትቀጥል አሰታውቀዋል። አምባሳደር ሰይድ በኩዌት በሚኖራቸው ቆይታ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ለሚሰሩት ስራ ድጋፍ እንደሚያደርጉም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል። አምባሳደሩ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተላከ መልዕክት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማቅረባቸውን ከኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በስርአት አልበኞች ላይ እየተወሰደ ያለው የህግ ማስከበር እርምጃ ከግብ እንዲደርስ ህዝቡ ትብብር ማድረግ አለበት--አፈ ጉባኤ ፋንታይቱ ካሴ 
Jun 4, 2023 116
ሰቆጣ ግንቦት 27/2015 (ኢዜአ) መንግስት በስርአት አልበኞች ላይ እየወሰደ ያለው ህግ የማስከበር እርምጃ ከዳር እንዲደርስ ህዝቡ አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ አለበት ሲሉ የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ገለጹ። የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ በሰቆጣ ከተማ ተካሂዷል። የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታይቱ ካሴ በጉባኤው ላይ እንደገለጹት፣ አገራዊ ሰላምን በማረጋገጥ የተጀመረውን ለውጥ ዳር ለማድረስ ሁሉም ለሰላም ትኩረት ሰጥቶ መረባረብ አለበት። ለውጡን የማይፈልጉ አንዳንድ ሃይሎች ሃሳብን በምክክር ማሸነፍ ሲያዳግታቸው እየሄዱበት ያለው ፓለቲካ ተቀባይነት የለውም፤ ህዝብንም ለከፋ ችግር ያጋልጣል ብለዋል። መንግስት በስርአት አልበኝነት የሚንቀሳቀሱትን አካላት ስርዓት ለማስያዝ እየወሰደ ላለው ህግ የማስከበር እርምጃ የብሔረሰብ አስተዳደሩ ምክር ቤቱ ድጋፍ እንደማይለየው ገልጸዋል። የህግ ማስከበር እርምጃው ግቡን እንዲመታም ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ እንዳለበትም አፈ ጉባኤዋ አስገንዝበዋል። በዞኑ በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የነበሩ ወገኖች በተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት ወደቄያቸው መመለሳቸውን የገለጹት አፈ ጉባኤዋ፣ በአካባቢውም ሰላም እየሰፈነ መምጣቱን ተናግረዋል።   ወደቄያቸው ለተመለሱ ወገኖች ባሉበት የሰብዓዊ ድጋፎችን ለማድረግ የሚመለከታቸው ተቋማት አስቸኳይ የምግብ እህል ድጋፍ እንዲያደርጉም በምክር ቤቱ ስም ጠይቀዋል። የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ ህብረተሰቡ ወደመደበኛ ህይወቱ በመመለስ የአካባቢውን ኢኮኖሚ እንዲያነቃቃ በተሰራው ሥራ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው፣ በቀጣይም ይሄ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመለክተዋል። ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴዎች በኩል የአስፈፃሚ አካላትን ዕቅድ አፈጻጸም እንቅስቃሴ ለማወቅ በመስክ ምልከታ ጭምር እያደረገ ያለው ክትትልና ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታይቱ አመለክተዋል። በዞኑ እየተስተዋለ ባለው ሥራ አጥነት፣ የኑሮ ውድነት፣ ብልሹ አሰራርና ሌብነት ህዝቡ እየተማረረ በመሆኑ በቀጣይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል። ምክር ቤቱ ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው ጉባኤ የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸምንና የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን እቅድ ክንውን እንደሚገምግም ተመልክቷል።    
ህብረተሰቡ መደበኛ ህይወቱን ያለስጋት መምራት እንዲችል የጸጥታ አካላት ሃላፊነታቸውን በብቃት ሊወጡ ይገባል-- መምሪያው
Jun 4, 2023 123
ሆሳዕና ግንቦት 27/2015 (ኢዜአ) ፡-ህብረተሰቡ መደበኛ ህይወቱን ያለስጋት መምራት እንዲችል የጸጥታ አካላት ሙያዊ ስነምግባር ተላብሰው የተጣለባቸውን ሀላፊነት በተሻለ ብቃት ሊወጡ እንደሚገባ የሀድያ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ አስታወቀ። በሀድያ ዞን ፖሊስ መዋቅር ላይ የተስተዋሉ ጉድለቶችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ያተኮረ ዞን አቀፍ የአመራር ግምገማ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው። የሀድያ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ በእዚህ ወቅት እንዳሉት የጸጥታ አካላት የህዝብን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅና የማስጠበቅ ሃላፊነት አለባቸው።   በመሆኑም ህብረተሰቡ መደበኛ ህይወቱን ያለስጋት መምራት እንዲችል የጸጥታ አካላት ሙያዊ ስነምግባር በመላበስ ሃላፊነታቸውን በተሻለ ብቃት ሊወጡ ይገባል ብለዋል። ስነምግባርን ተላብሶ አገልግሎት በመስጠት በኩል በዞኑ ባሉ የጸጥታ መዋቅሮች የተስተዋሉ መጠነኛ ችግሮች እንዳሉ ገልጸው፣ ዞኑ ችግሮችን ለይቶ ለማረም እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የግምገማ መድረኩም የዜጎችን ደህንነትና ሰላም በማስጠበቅ ተግባር በተለይ በአንዳንድ የጸጥታ አካላት ላይ የሚስተዋለውን ችግር ለመፍታት ያለመ መሆኑን አስረድተዋል። ለሦስት ቀናት በሚቆየው የግምገማ መድረክ በተለይም በሆሳዕና ከተማና በሌሎች አካባቢዎች ከንጥቂያ፣ ዝርፊያና መሰል እየተበራከቱ ያሉ ወንጀሎችን ለማስቀረት የሚያስችል የጋራ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም አቶ ሳሙኤል ተናግረዋል። ከእዚህ በተጨማሪ ሃላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡትን በመለየት አስፈላጊ እርምጃ እንደሚወሰድና ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም ገልጸዋል። የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ዋና ሳጅን ተሾመ ባቲሶ በበኩላቸው፣ የዞኑ የፖሊስ መዋቅሮች በወንጀል ቅድመ መከላከልና ፍትሀዊ አገልግሎት በመስጠት በኩል ውስንነት እንዳለባቸው ገልጸዋል። "ከህዝብና ከመንግስት የተሰጠን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት ሲገባ ኃላፊነትን ወደጎን በመተው የግል ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ የሚሰሩ የፖሊስ አባላት ስለመኖራቸው በተለያየ መንገድ ለማወቅ ተችሏል" ብለዋል። ባልተገባ ተግባር በመሳተፍ ላይ የሚገኙ አባላትን በመለየት ተገቢ የሆነ እርምትና እርምጃ ለመውሰድ የግምገማ ውጤት እየተጠበቀ መሆኑንም ጠቁመዋል።   በዞኑ ፖሊስ መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ሳህሉ ኃይሌ በበኩላቸው እንዳሉት፣ ፖሊስ የአካባቢንና የማህበረሰቡን ሰላም የማስጠበቅ ሀገራዊ ኃላፊነት ተሰጥቶታል። ይሁንና ፖሊሳዊ ስነ ምግባርንና መርህን ተከትሎ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ በኩል ውስንነት እንዳለበት ተናግረዋል። "የማህብረሰቡን ሰላም አጠናክሮ የማስጠበቅ ሃላፊነቱን በአግባቡ በመወጣት በኩል ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የመድረኩ አስፈላጊነት ከፍተኛ ነው" ብለዋል። የፀጥታ አካላት ሙያዊ ስነ ምግባር በመላበስና ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ለአካባቢ ስጋት የሆኑ የጸጥታ ችግሮችን ለማስቀረት መስራት እንዳለባቸው የተናገሩት ደግሞ በመምሪያው የስታፍ ዲቪዥን ኃላፊው ኢንስፔክተር አብርሃም ቀጭኔ ናቸው። እንደእሳቸው ገለጻ፣ ማህበረሰብን ያሳተፈ የወንጀል መከላከል ተግባር የማህበረሰቡን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማስቀጠል ጠቀሜታው የጎላ ነው። በመድረኩ በዞኑ ከሚገኙ ከሁሉም የገጠር ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች የሰላምና ፀጥታና እንዲሁም የፖሊስ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው።  
ማህበራዊ
በሲዳማ ክልል ማረሚያ ቤቶች  ያለው የታራሚዎች  መልካም አያያዝ  ተጠናክሮ መቀጠል አለበት - ቋሚ ኮሚቴው
Jun 5, 2023 42
ሀዋሳ ግንቦት 28 /2015 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ማረሚያ ቤቶች በታራሚዎች አያያዝ ዙሪያ ያለውን መልካም ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው ዛሬ የሀዋሳ ማዕከላዊ ማረሚያ ተቋምንና በሀዋሳ ከተማ የመሀል ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያን ተመልክቷል። በዚህ ወቅት የቋሚ ኮሚቴው ቡድን መሪ ወይዘሮ ዘሀራ ቢፍቱ፤ በማረሚያ የሚገኙ ታራሚዎች ሰብዓዊ መብቶቻቸው ተከብሮላቸውና አስፈላጊ መሰረታዊ አቅርቦቶች እንደተሟሉላቸው ከምልከታቸው መረዳታቸውን ገልጸዋል። ለታራሚዎቹ የምግብ፣ የህክምና አገልግሎትና ትምህርት ከአንደኛ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እየተማሩ እንደሚገኙ፤ በማረሚያው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስዶ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባት የቻለ ታራሚ እንዳለ ማወቅ መቻላቸውን ጠቅሰዋል። በተለያዩ መስኮች በማህበር ተደራጅተው ስራ እንዲሰሩና ገቢ አግኝተው ከራሳቸው ባለፈ ቤተሰቦቻቸውን መደጎም የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩንም መረዳት እንደቻሉ ጠቁመዋል። በአጠቃላይ በማረሚያው ያለው የሰብዓዊ መብት አያያዝ መልካም ሁኔታ ለሌሎችም ተሞክሮ መሆን የሚችል እንደሆነ ገልጸው፤ ከማደሪያ ቤቶች አንጻር ጥበት መኖሩ እንደክፍተት የታየ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል። በማረሚያ ቤቱ ባየነው ነገር ተደስተናል፤ በቀጠሮ የሚመላለስ እንደሌለ ተረድተናል ያሉት ቡድን መሪዋ፤ ከይቅርታና ምህረት ጋር ተያይዞ ያለው ቅሬታ ለመፍታት ጥናት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የሲዳማ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ኮንታሞ ቡርቃ በበኩላቸው፤ ክልሉ ከተመሰረተ ሶስት ዓመት እድሜ እንዳለውና ከዕድሜው አንጻር ያሉት ሁለት ማረሚያ ቤቶች ብቻ በመሆናቸው የታራሚዎች ቁጥርና ማደሪያ ክፍል አለመጣጣም እንደሚታይ አስረድተዋል። በማረሚያ ቤቱ ከለውጡ በፊት በነበረው ሁኔታ በታራሚዎች ላይ በኮሚሽኑ ፖሊሶች ይደርስ የነበረ ሰብዓዊ መብት ጥሰትን ከታራሚዎችና ከፖሊስ ሀይሉ ጋር በመነጋገር ጥፋቶችን በመለየት እርምጃ በመወሰዱ ማስቀረት ተችላል ብለዋል። በማረሚያ ቤቱ ከሚገኙ የህግ ታራሚዎች ውስጥ አስተያየቱን የሰጠው የታራሚዎች ኮሚቴ ጸሀፊ አዳነ ለማ እንዳለው፤ ከለውጡ በፊት በታራሚዎች ላይ ይደርስ የነበረው በደልና የመብት ጥሰት ቀርቷል። አሁን ሁሉም ነገር ተለውጦ ታራሚው መብቱ ተከብሮለት በጥሩ ሁኔታ የእርማት ጊዜውን እንደሚያጠናቅቅም ገልጿል።  
በደቡብ ክልል የኮሌራ በሽታ ተጋላጭነትን ለመቀነስ ግንዛቤን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
Jun 5, 2023 43
ዲላ ግንቦት 28/2015 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ክልል የሚታየውን የኮሌራ በሽታ ስርጭትና ተጋላጭነት ለመቀነስ የኅብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ከመገናኛ ብዙሃን አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በበሽታው ስርጭት ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠርን ዓላማ ያደረገ የውይይት መድረክ ዛሬ በዲላ ከተማ አካሂዷል። በቢሮው የማህበረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ወንድዬ በሽር በመደረኩ እንዳሉት የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት በሽታውን በመከላከልና በመቆጣጠር ተግባር ሚናቸውን መወጣት አለባቸው። በተለይም በክልሉ በሚገኙ አንዳንድ ቦታዎች የታየውን ስርጭት ለመግታት ቢሮው ከሌሎች ባለድርሻ አካላትና ማህበረሰብ ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል። ባለፉት አምስት ቀናት በተካሄደ የክትባት ዘመቻ 178 ሺህ በላይ ዜጎች መከተባቸውንና ሌሎች የጤና አገልግሎት ተደራሽ እየተደረጉ መሆናቸውን ከፍተኛ ባለሙያው አስረድተዋል። በክልሉ የበሽታው ምልክቶች ከታየባቸው 2 ሺህ 511 ዜጎች ውስጥ ከ93 በመቶ የሚልቁት የሕክምና አገልግሎት አግኝተው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ተናግረዋል። ለበሽታው ያለውን ተጋላጭነት ለመግታት የህብረተሰቡን የንጽህና አጠባበቅ ግንዛቤ ለማሳደግ የጋራ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አቶ ወንድዬ አስገንዝበዋል። የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ህብረተሰቡ የራሱንና የአካባቢውን ንጽህና እንዲጠብቅ በማስተማር ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል። ''የበሽታውን ስርጭት ለመግታት የተቀናጀ ምላሽ ያስፈልጋል'' ያሉት ደግሞ የክልሉ ጤና ቢሮ የኮሙኒኬሽን ሃላፊ አቶ ቀዲሬላ አህመድ ናቸው።   በተለይ ለህብረተሰቡ የንጹህ ውሃ ተደራሽነትን ከማሳደግ ባለፈ፤ በሽታውን በዘላቂነት እንዲከላከል ግንዛቤውን ማሳደግ ይገባል ብለዋል። በክልሉ የክረምት ወቅትን ተከትሎ ለወረርሽኙ ምቹ ሁኔታ እንዳይፈጠር የጥንቃቄ ሥራዎች እንዲከናወኑም ጠቁመዋል። በተለይ የተበከለ ፈሳሽና ደረቅ ቆሻሻ ለበሽታው መስፋፋት ምክንያት ስለሚሆኑ ህብረተሰቡ ለግልና አካባቢ ጽዳት አጠባበቅ ትኩረት እንዲሰጥ በተቀናጀ መንገድ ትምህርት እየተሰጠ ነው ብለዋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ሥራ አስኪያጅ መምህር አስናቀ እንድሪያስ መድረኩ በበሽታው ስርጭት ዙሪያ ወቅታዊ መረጃ የሰጠ፣ በሽታውን ስርጭት ለመግታት የመገናኛ ብዙሃን ሚና ያመላከተ መሆኑን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ በሚረዳው መልኩ በማስተማር ከበሽታው እንዲጠበቁ ሙያዊ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።  
በኢትዮጵያ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ የቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል ተገኘ
Jun 5, 2023 55
አርባ ምንጭ ግንቦት 28/2015 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ የቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል መገኘቱን አንድ ዓለም አቀፍ የተመራማሪ ቡድን አስታወቀ። 12 አባላትን የያዘው ዓለም አቀፍ የቅሪተ አካል ተመራማሪ ቡድን በባሌ ተራሮች ስር ባካሄደው ተከታታይ አምስት ዓመታትን በፈጀ ጥናት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዕድሜ ያስቆጠረ የቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል ማግኘቱን ገልጿል። በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የታሪክና ቅርስ ጥናት ትምህርት ክፍል አዘጋጅነት በተገኘው ቅሪተ አካልና የጥናት ሂደቱን የተመለከተ ለተለያዩ አካላት ገለጻ ተደርጓል። በውይይቱ ላይ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና በእሥራኤል አገር ሂብሪው ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም ቅሪተ አካሉን ያገኘው ተመራማሪዎች ቡድን አስተባባሪ ዶክተር ተገኑ ጎሳ ጥናቱንና ግኝቱን የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚህም ቡድኑ በባሌ ሰንሰለታማ ተራሮች ግርጌ ስር ባደረገው ጥናት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዕድሜ ያለው የቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል መገኘቱን አረጋግጠዋል። ቅሪተ አካሉ የተገኘው በፈረንጆች አቆጣጠር በ2017 ዓ.ም ሲሆን የግኝቱ ትክክለኝነት የበለጠ ለማጠናከር ተጓዳኝ የጥናት ሂደቶች ሲከናወኑ ቆይተው ግኝቱ ይፋ ሆኗል ብለዋል። በጥናቱ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ ያለው የቀይ ቀበሮ ግማሽ የመንጋጋው ክፍል የተገኘ መሆኑን አረጋግጠው እስከ ቅርብ ጊዜ የተለያዩ ጥናቶች ሲደረግበት መቆየቱን ገልጸዋል። ይህም ይበልጥ ጥናቱ ጎልብቶ የተረጋገጠ መረጃ ለዓለም ለማበርከት ሲባል መሆኑን ገልጸው ሂደቶቹ መጠናቀቃቸውን ተከትሎ ዛሬ ይፋ መደረጉን ነው የተናገሩት። በዚሁም ቅሪተ አካሉ አሁን ካሉ የቀይ ቀበሮዎችና መሰል እንስሳት ጋር ያለው አንድነትና ልዩነት እንዲሁም የዕድሜና ሌሎች ጥናቶች መደረጋቸውን አስረድተዋል። ቀይ ቀበሮዎቹ በሀገራችን በሰሜንና ባሌ ተራሮች አካባቢ የሚገኙ ሲሆን ህብረተሰቡ ለግጦሽና ለእርሻ መሬት ፍለጋ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ብሎም ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተዳምሮ የዱር አራዊቱ በአሁኑ ሰዓት የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበት መሆኑን አስገንዝበዋል።   የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዝዳንት ተባባሪ ፕሮፈሰር በሃይሉ መርደኪዮስ፣ ግኝቱ ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ በሌሎች ዓለማት የማይገኙ የዱር እንስሳት ባለቤት መሆኗን ለማረጋገጥ ተጨማሪ አቅም የሚሆን ማስረጃ መሆኑን ገልጸዋል። የመርሃ ግብሩ ዓላማም በመጥፋት ላይ ያለውና ብቸኛ የሆነው ቀይ ቀበሮ ቅሪተ አካል መገኘቱን ለህዝብ ይፋ ለማድረግ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመሆኑም መንግስትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት ዝሪያውን ከመጥፋት መታደግ እንዳለበትም ጠቁመዋል። ይህ ግኝት በኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች አስተባባሪነት የተገኘ መሆኑን ያስታወሱት ደግሞ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባህልና ቋንቋ ጥናት ተቋም ዳይሬክተር ዶክተር ሰይድ አህመድ ናቸው። በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ብርቅዬ እንስሳት ለቱሪዝም ክፍለ ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ጠቅሰው ለዝሪያቸው አስፈላጊው ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባም አመልክተዋል። በዚህ ረገድ ዩኒቨርሲቲው እንደ ከፍተኛ ተቋም በጥናት የተደገፈ መረጃ በመስጠት የማንቃትና ሌሎች ሃላፊነቶች እየተወጣ መሆኑንም አብራርተዋል። ጥናቱ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ2013 እስከ 2017 ዓ.ም ተከታታይ ዓመታት የፈጀ ሲሆን በዚሁም ሁለት ኢትዮጵያዊያን ጨምሮ 10 የተለያዩ ሀገራት ተመራማሪዎች በአጠቃላይ 12 ዓለም አቀፍ ተመራማሪዎች መሳተፋቸው ተመላክቷል፡፡    
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሀብት ብክነትን ለመቀነስና የአሰራር ሥርዓት ለማሻሻል ጥረት እየተደረገ ነው-  የዩኒቨርሲቲው  ከፍተኛ አመራሮች
Jun 5, 2023 47
  ዲላ ግንቦት 28/2015 (ኢዜአ) --የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሃብት ብክነትንና ለመቀነስና የአሰራር ሥርዓትን በማሻሻል ብልሽቶችን ለማረም እየሰራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ፡፡ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ዩኒቨርሲቲውን በቀጣይ የራስ ገዝ ለማድረግ ምቹ መደላድል የሚፈጥሩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውንም ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ፍቃዱ ወልደማሪያም እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው በኦዲት ግኝት የተለዩና ሌሎች ችግሮችን ለማስተካከል እየተሰራ ነው። በዚህም ብልሽቶችን በማረም አመራሩን ሪፎርም ከማድረግና ተጠያቂነትን ከማስፈን ጀምሮ የአሰራር ሥርዓቱን እስከ ማሻሻል የዘለቁ ተግባራት እየተካሄዱ ነው ብለዋል። በሁሉም የትምህርት ክፍሎች የሚታዩ ድክመቶችንና ጥንካሬዎችን በጥናት በመለየት የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑንም ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል። በተለይም ብልሽቶች ገነው በወጡባቸው በግንባታ ፕሮጀክቶችና በተማሪዎች አገልግሎት የሚታዩ ችግሮችን በመለየት የሕግ ተጠያቂነትን የማረጋገጥና የተመዘበረ ሃብት የማስመለስ ሥራዎች እየተካሄዱ መሆናቸውን አስረድተዋል። ለተቋም ግንባታ የሰው ኃይል ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፣ በሰው ሃብት አስተዳደርና ልማት ላይ የታዩ ብልሽቶች እስኪታረሙ በጊዜያዊነት ቅጥርና ምደባ እንዲቆም መወሰኑን አስታውቀዋል።   በዩኒቨርሲቲው እየተከናወኑ ያሉ የለውጥ ሥራዎች ብልሽቶችን በማረም ለኦዲት ግኝት ምላሽ ከመስጠት ባለፈም፤ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ ለማድረግ የጸደቀውን ዓዋጅ ለመተግበር አቅም እንደፈጠረ አመላክተዋል። በተለይ የሃብት ብክነትን ለመቀነስና የአሰራር ሥርዓት በማሻሻል ክፍተቶችን በዘላቂነት ለማረም እየተሰራ መሆኑን ዶክተር ፍቃዱ ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተከናወኑት የዳታ ማዕከል፣ የመምህራን መኖሪያ ቤቶችና መሰል የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ የግዥ ብቻ ሳይሆን፣ የፕሮጀክት አስተዳደር ችግር እንዳለባቸው ያነሱት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የቢዝነስና ተቋማዊ ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ዳራሪ ሰናይ ናቸው። የዘገዩ፣ የግንባታ ውልና የመረካከቢያ ሰነድ የሌላቸው በሚል ፕሮጀክቶችን በስድስት ዘርፎች በመከፋፈል በተቋም አቅምና በባለድርሻ አካላት የማጥራት ሥራ መከናወኑን አስረድተዋል።   በዚህም የመንግሥትን የግዥና ንብረት አስተዳደር ዓዋጅን ባልተከተሉና ችግር ያለባቸው የግንባታና አማካሪዎች ጋር የነበሩ ውሎች ሙሉ በሙሉ እንዲቆሙ መደረጉን አስታውቀዋል። በተለይ የተጋነኑ የግዥ ውሎችን በመሰረዝና አማካሪ ድርጅቶችን በማገድ የመንግሥትና የዩኒቨርሲቲውን ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ ለህጋዊ ተቋራጮች መተላለፋቸውን ምክትል ፕሬዚዳንቱ አብራርተዋል፡፡ በዚህም የዘገዩ የመምህራን ቤቶች ግንባታና መለስተኛ ስታዲዬም ግንባታቸው ተጠናቅቆ ለአገልግሎት መብቃታቸውን ገልጸዋል። የዩኒቨርሲቲውን አሰራር ችግሮች በማረም ቁመናውን ከማስተካከል በላይ የራስ ገዝ አስተዳደርን እውን የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል። በተለይ የፋይናንስ ነጻነትን ለማረጋገጥ ዓዋጁን መሠረት ያደረጉ የገቢ አቅም ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ኢንጂነር ዳራሪ አስታውቀዋል። በዩኒቨርሲቲው በኦዲት ግኝት የተለየ ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብና ለሌሎች ብልሹ አሰራሮች እንዲስተካከሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅጣጫ ማስቀመጡ የሚታወስ ነው።    
ኢኮኖሚ
የሰኔ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል--የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር
Jun 5, 2023 38
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015 (ኢዜአ)፣- የሁሉም ነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከግንቦት 29 ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በግንቦት ወር ሲሸጥ በነበረው ዋጋ እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ መንግሥት ባለፉት አመታት ከነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋን ሲደጉም ቆይቶ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ውስጥ ያሉት ዜጎችን ያደረገ ስራ ሲሰራ ቆይቷል። በዚሁ አግባብ የነዳጅ ድጎማን ደረጃ በደረጃ ለማስቀረትና ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ጨምሮ ለዓመታት የተከማቹ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል ሪፎርም በተያዘው በጀት ዓመት በመጀመር እየተተገበረ መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡ በመሆኑም ዝቅተኛ ገቢ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል ታሳቢ ያደረገው የታለመ ድጎማ አፈጻጸም በተጨማሪ በነዳጅ ግብይት ዙሪያ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲቻል ማንኛውም በነዳጅ ማደያዎች የሚደረግ ግብይት በዲጂታል ክፍያ ብቻ እንዲፈጸም በማድረግ በሀገር ደረጃ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብሏል፡፡ ስለሆነም የታለመ የነዳጅ ድጎማንም ሆነ የነዳጅ ዲጂታል ግብይት ትግበራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ሆኖ በነዳጅ ማደያዎች ይህንን ትግበራ በማደናቀፍ ህገ-ወጥ ተግባራትን የሚፈጽሙ አካላትን ላይ የተጠናከረ እርምጃ በየደረጃው የሚወሰድ መሆኑም አስታውቋል። በየደረጃው የሚገኝ የመንግስት መዋቅርና የጸጥታ አካላት እንዲሁም ህብረተሰቡ በታለመ ድጎማ ሰበብ የሚፈጸም ህገ-ወጥ ተግባርና በካሽ የሚፈጸም የነዳጅ ግብይት ላይ ተገቢውን ክትትል እና ቁጥጥር እንዲያደርጉ ሲል ሚኒስትር መስራ ቤቱ አሳስቧል፡፡ በዚሁ መሠረት፦ 1. ቤንዚን ……………………………………… ብር 69.52 በሊትር 2. ነጭ ናፍጣ…………………………………… ብር 71.15 በሊትር 3. ኬሮሲን ……………………………………... ብር 71.15 በሊትር 4. የአውሮፕላን ነዳጅ …………………………. ብር 65.35 በሊትር 5. ቀላል ጥቁር ናፍጣ………………………….. ብር 57.97 በሊትር 6. ከባድ ጥቁር ናፍጣ………………………….. ብር 56.63 በሊትር መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡
በምሥራቅ ጎጃም በመስኖ ከለማው የበጋ ስንዴ ከ881 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ተሰበሰበ - የዞኑ ግብርና መምሪያ
Jun 5, 2023 46
ደብረ ማርቆስ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ):- በምስራቅ ጎጃም ዞን በበጋ ወራት በመስኖ ከለማው የስንዴ ማሳ እስካሁን ከ881 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የመስኖ ልማት የሥራ ሂደት ቡድን መሪ አቶ ሃብታሙ አሕመድ ለኢዜአ እንደተናገሩት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ አርሶ አደሮችንና ባለሙያዎችን ያሳተፈ የተቀናጀ ርብርብ ተደርጓል። በዚህም በዘንድሮው በጋ ከ100 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ21 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ በመስኖ መልማቱን ገልጸዋል።   ከለማው ማሳ ላይም ከ920 ሺህ ኩንታል በላይ ስንዴ ለመሰብሰብ ታቅዶ እስካሁን በተደረገ ጥረት ከ881 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን አስታውቀዋል። በዞኑ በበጋ የመስኖ ስንዴ ልማት ከተጀመረ ሁለት ዓመታት እንደሆነው የተናገሩት የቡድን መሪው፣ በዚህ ዓመት የለማው መሬት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ17 ሺህ ሄክታር መሬት ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል። የበጋ ስንዴ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ በኩታ ገጠም የተደራጁ አርሶ አደሮች ከ6ሺህ በላይ የውሃ መሳቢያ ሞተሮችን ጥቅም ላይ ማዋላቸውን አስረድተዋል። በልማቱ ከተሳተፉ አርሶ አደሮች መካከል በእነማይ ወረዳ የማህበረ ብርሃን ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ተስፋው ገላዬ በሰጡት አስተያየት ዘንድሮ ግማሽ ሄክታር መሬት በማረስ ከ23 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል። ካመረቱት ስንዴም ከ15 ኩንታል በላይ የሚሆነውን ሸጠው ከ60 ሺህ ብር በላይ እንዳገኙ አስታውቀዋል። የጎዛምን ወረዳ የጥጃን ቀበሌ ነዋሪው አርሶ አደር አስናቀ እንደግ በበኩላቸው በበጋ ስንዴ ልማቱ በመሳተፍ ምርታማነታቸውን እንዳሳደጉ ተናግረዋል። ወደ መስኖ ልማቱ ለመግባት እየተጠራጠሩ እንደ ጀመሩ ያስታወሱት አርሶ አደሩ፣ ከሩብ ሄክታር በላይ ማሳ በማረስ 18 ኩንታል ምርት በማግኘታቸው ግን ጥርጣሬያቸው እንደተወገደ ገልጸዋል።      
የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በዝቅተኛ ደረጃ የሚገኙ ዜጎች ህይወት እያሻሻለ ነው
Jun 5, 2023 52
ሰቆጣ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ) በአማራ ክልል የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ህይወት በማሻሻል ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከቱን የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ የልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የሚተገበርባቸው 17 ከተሞች የስራ ሃላፊዎች በሰቆጣና ላለቢበላ ከተሞች በከተማ ፕሮግራሙ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። የክልሉ የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ሱሌማን እሸቱ በጉብኝቱ ላይ እንደገለጹት የከተሞች ልማታዊ ሴፍትኔት በተለይም በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ከተሞች መልካም አጋጣሚ የፈጠረ ነው። በዚህም በላሊበላና በሰቆጣ ከተሞች በፕሮግራሙ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን እንቅስቃሴ በማስጎብኘት የተሞክሮና ልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ማስቻሉን ገልጸዋል። በመስክ ጉብኝቱም በክልሉ ፕሮግራሙ የሚተገበርባቸው ከ17 ከተሞች የተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎችና የስራ ሃላፊዎች መገኘታቸው ግቡን ለማሳካት የሚያስችል ነው ብለዋል። በክልሉ በልማታዊ ሴፍቲኔት ከታቀፉት ከ100 ሺህ በላይ ዜጎች ውስጥ 80 ሺህ የሚሆኑት በከተሞች ፅዳትና ውበት ዘርፍ በመሰማራት የከተሞችን ገጽታ በመገንባት ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል። በተጨማሪ የገቢ ማስገኛ በጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም አነስተኛ ንግድ ስራዎች በመሰማራት በአጭር ጊዜ ኑሯቸው እንደሚሻሻል በሰሩት ስራ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን አስረድተዋል። በተጨማሪም አቅመ ደካሞችና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ከ20 ሺህ በላይ የሚሆኑ ወገኖችን ደግሞ በቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን አስገንዝበዋል። እንደ አቶ ሱሌማን ገለፃ ፕሮግራሙ ከተጀመረ ወዲህ በክልሉ በዝቅተኛ ደረጃ የሚገኙ ዜጎችን ህይወት በማሻሻል ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ገልፀዋል። የጎንደር ከተማ የምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔት ፅህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ ሃድያ መሃመድ እንዳሉት የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ከ2014 ዓ.ም ታህሳስ ወር ጀምሮ በከተማቸው መተግበር መጀመሩን ተናግረዋል።   በአሁኑ ወቅትም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ከ23 ሺህ በላይ ዜጎች በአካባቢ ልማትና በቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በማከል። በመሆኑም የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎች የስራ ባህልና የቁጠባ ባህላቸው እንዲያድግ ማድረጉን ነው ወይዘሮ ሃድያ የገለፁት። የደሴ ከተማ የምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔት ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ብርሃኑ ሙሴ በበኩላቸው የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም መተግበር ከተጀመረ ወዲህ የተጠቃሚው ህይወት እየተሻሻለ መጥቷል ብለዋል። በዚህም በፕሮግራሙ በመጀመሪያው ዙር ታቅፈው የነበሩ 15 ሺህ 547 ዜጎች ማስመረቅ መቻሉን ጠቁመው በሁለተኛ ዙርም 4 ሺህ 767 ዜጎች በከተማቸው የአካባቢ ልማትና እንክብካቤ ላይ እየሰሩ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። በተለይም በመጪው ክረምት በከተማዋ የጎርፍ አደጋ እንዳያጋጥም ቦዮችን በማጽዳት፣ የፈረሱትን በመጠገንና አዳዲስ መከላከያ ቦዮችን በመገንባት የህብረተሰቡን ደህንነት ለመጠበቅ መስራታቸውን አስረድተዋል። ለፕሮግራሙ ስራ ማስኬጃ በተያዘው ዓመት የ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በጀት ተይዞ በክልሉ በ17 ከተሞች እየተተገበረ ይገኛል።    
አውደ-ርዕዩ የግብርና ዘርፉን ውጤታማነት ማጠናከር የሚያስችል ውጤት የተገኘበት ነው - የግብርና ሚኒስቴር
Jun 5, 2023 59
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015 (ኢዜአ)፦ የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ የዘርፉን ውጤታማነት ማጠናከር የሚያስችል ውጤት የተገኘበት መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። በሳይንስ ሙዚየም ሲካሄድ የነበረው የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ ከ88 ሺህ በላይ ሰዎች መጎብኘት መቻላቸውንም ሚኒስቴሩ ገልጿል። በሳይንስ ሙዚየም ለአንድ ወር “ከቤተ-ሙከራ ወደ አዝመራ” በሚል መሪ ሐሳብ ሲካሄድ የነበረው የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ በትላንትናው እለት ተጠናቋል። አውደ-ርዕዩ የግብርና ዘርፉን ውጤታማነት ማጠናከር የሚያስችል ውጤት የተገኘበት ሆኖ መጠናቀቁ ተገልጿል። ትላንት በተካሄደው የአውደ-ርዕዩ መዝጊያ ሥነ-ሥርዓትም አስተዋጽዖ ላደረጉ አካላት እውቅናና ሽልማት ተበርክቷል።   የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ የተሳካ ዓላማዎቹና ግቦቹን ያሳካ ነው። በዚህም የግብርና ዘርፉን ውጤታማነት ማጠናከር የሚያስችል ውጤት የተገኘበት አውደ-ርዕይ መሆኑን ጠቁመዋል። ግብርናው ከየት ተነስቶ የት እንደ ደረሰ፣ ግብርናውና የግብርና ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም ፈጠራዎች የደረሱበትን ሁኔታ ለማሳየት በተካሄደው የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ ጠቃሚ ውጤቶች መገኘታቸውን ነው ሚኒስትሩ የገለጹት። ከግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ ጎን ለጎንም የስንዴ ልማት ውጤታማነት፣ የሌማት ትሩፋት፣ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሥራዎችና ዲጂታል ግብርና ላይ ያተኮሩ የፓናል ውይይቶችም እንደተካሄዱ ዶክተር ግርማ አመንቴ አክለዋል። አውደ-ርዕዩ በተለይም የግብርናው ዘርፍ የደረሰበት ደረጃ የተመላከተባቸው፣ ዘርፉን ማሳደግና የተገኙ ስኬቶችን ማጠናከር የሚያስችሉ አራት አውደ-ጥናቶች መካሄዳቸውን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ሌሎች ግብርናውን አጋዥ የሆኑ ዘርፎችን ያካተተ አውደ-ርዕይ በቋሚነት እንዲካሄድ ጥያቄዎች መነሳታቸውንም ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫ ጠቁመዋል። የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ ለሕዝብ ተደራሽ እንዲሆን መገናኛ ብዙኃን ለሰጡት ሽፋን ምስጋና ያቀረቡት የግብርና ሚኒስትሩ፤ በቀጣይ የተሻለ የግብርና አውደ-ርዕይ ለማዘጋጀት በቂ ልምድ እንደተገኘበት ገልጸዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በጎንደር ከተማ ወጣቶች ከወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችና ከእምቦጭ አረም ቁሶችን በማምረት የስራ እድል እየፈጠሩ ነው
Jun 5, 2023 41
ጎንደር ግንቦት 28/2015 (ኢዜአ) በጎንደር ከተማ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችንና የእምቦጭ አረምን በግብአትነት ተጠቅመው የመገልገያ ቁሶችን አምርተው በመሸጥ ለገቢ ማግኛ ማዋላቸውን በስራ ፈጠራ የተሰማሩ ወጣቶች ገለጹ፡፡ በሀገራችን ለ30ኛ ጊዜ እየተከበረ ያለው የዓለም አካባቢ ቀን "የፕላስቲክ ብክለትና መፍትሄዎች’’ በሚል መሪ ሐሳብ በጎንደር ከተማ በፓናል ውይይትና በዐውደ ርእይ ዛሬ ተከብሯል፡፡ የፕላስቲክ ብክለትን ለማስቀረት የሚያስችሉ ስራዎችን ሰርተው በዐውደ ርዕዩ ላይ የስራ ውጤታቸውን ያቀረቡ ወጣቶች እንዳሉት በአግባቡ ከተጠቀምንባቸው ወዳድቀው የሚጠፉ ቁሶች እምብዛም አይኖሩም። የከተማዋ ነዋሪ የሆነው ወጣት ምስጋናው ጀንበሬ እንደገለጸው ከወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶች መጥረጊያና ገመዶችን በመስራት በዐውደ ርእዩ ላይ ለእይታ አቅርቧል። አምስት ሆነው የጀመሩት ስራ አሁን ላይ ለ15 ተጨማሪ ለስራ ፈላጊ ወገኖች የስራ እድል በመፍጠር በቀን 800 የወዳደቁ የውሃ ፕላስቲኮችን በመሰብሰብ ጥቅም ላይ እያዋሉ መሆናቸውን አስረድቷል፡፡ በቀን እስከ 40 የፕላስቲክ መጥረጊያዎችን አምርተው ለገበያ አቅርበው በመሸጥ ራሳቸውንና በስራቸው የቀጠሯቸውን ግለሰቦች ተጠቃሚ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ በማከል። በዚህም የፕላስቲክ ተረፈ ምርትን ጥቅም ላይ በማዋል የከተማውን ጽዳትና ውበት ከመጠበቅ ባሻገር በግድቦችና ጎርፍ መፋሰሻ ቦዮች ላይ ይደርስ የነበረውን ብክለት ማስወገድ መቻላቸውን አስገንዝበዋል። በጣና ሀይቅ ህልውና ላይ የአደጋ ስጋት ደቅኖ የቆየውን የእምቦጭ አረም አድርቀውና ፈጭተውም አካባቢውን በማይበክል መንገድ ለወረቀት ስራ እየተጠቀሙበት ያሉት ደግሞ እነ ወጣት ሰለሞን ብርሃኔ ናቸው፡፡ የእምቦጭ አረምና የተጣሉ ቆሻሻ ወረቀቶችን በጥሬ እቃነት በማዋል የእቃ መያዣ ዘንቢሎችን፣ የሰርግ የጥሪ ካርዶችና የፋይል ማቀፊያዎችን በመስራትና በመጠቀም ለ20 ሴት ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር እንደቻሉም አስረድቷል፡፡ በቀን አምስት ኩንታል የእምቦጭ አረምን በጥሬ እቃነት መልሶ በመጠቀም የአካባቢን ብክለት እየታደጉ መሆናቸውን ጠቁሞ፤ ወደፊትም ስራውን በፋብሪካ ደረጃ ለማስፋት እቅድ እንዳላቸው ተናግሯል፡፡ የጎንደር ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ጽዳትና ውበት አረንጓዴ ልማት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ምስጋናው ጀንበሬ በበኩላቸው በከተማው በአራት ማህበራት የተደራጁ ከ200 በላይ ወጣቶች ቆሻሻን መልሰው ጥቅም ላይ እያዋሉ ይገኛሉ፡፡ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ጥቅም ላይ ለማዋል በሚያስችሉ የስራ ፈጠራ ለተሰማሩ ወጣቶችና ኢንተርፕራይዞች የሙያ ስልጠና ከማመቻት ጀምሮ የፋይናንስ ድጋፍ እንዲያገኙ መደረጉን አስረድተዋል፡፡ በጎንደር ከተማ ባለፉት 10 ወራት ከ145ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ደረቅ ቆሻሻን በማስወገድ የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ ጥረት መደረጉንም ሃላፊው አስረድተዋል፡፡    
በአገር አቀፍ ደረጃ የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ማዕከላት ለማስፋት ትኩረት ተደርጓል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
Jun 5, 2023 44
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦በአገር አቀፍ ደረጃ የሥራ ፈጠራ ክህሎትን ለማስፋት የሚያስችሉ የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ማዕከላት ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ። "ብሩህ ኢትዮጵያ" የንግድ ሥራ ፈጠራ ኃሳብ ውድድር ተሳታፊዎች በቡራዩ ተሰጥዖ ማበልፀጊያ ትምህርት ቤት ሥልጠና መሰጠት ተጀመረ።   ለ"ብሩህ ኢትዮጵያ" የንግድ ሥራ ፈጠራ ኃሳብ ውድድር ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የመጡ 200 ተወዳዳሪዎች ተመልምለዋል። ተሳታፊዎቹ ከዛሬ ግንቦት 28/2015 ዓ.ም እስከ ሰኔ 17/2015 ዓ.ም የሚቆይ ሥልጠና በቡራዩ ተሰጥዖ ማበልፀጊያ ትምህርት ቤት መከታተል ጀምረዋል። ሥልጠናው በሥራ ፈጠራ፣ ኃሳብን ወደ ተግባር መቀየርና የንግድ አመሰራረትን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተገልጿል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የመርኃ ግብሩ ዓላማ ማሰልጠን፣ መሸለምና ማብቃት ነው።   መርኃ ግብሩ ክትትልና ድጋፍን የሚያካትት መሆኑን ገልጸው የፈጠራ ኃሳቦች ወደ ተግባር ተቀይረው ሕዝብና አገር እንዲጠቅሙ ታስቦ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እስካሁን ባሉ ውድድሮች ተወዳድረው በየደረጃው ያሉ አሸናፊዎች የፈጠሯቸው ኢንተርፕራይዞች ተስፋ ሰጭ ጅምሮችን እያሳዩ እንደሚገኙ አመላክተዋል። ለሰባት ተከታታይ ጊዜያት በተካሄደው "ብሩህ ኢትዮጵያ" የንግድ ሥራ ፈጠራ ኃሳብ ውድድር አሸናፊ ለሆኑ 381 ዜጎች ቋሚ የሥራ እድል መፍጠሩንም ጠቁመዋል። በአሁኑ ውድድር ለሚያሸንፉ 50 ባለ ኃሳቦች ለሥራ መነሻ የሚሆን ለእያንዳንዳቸው የአምስት ሺህ ዶላር ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተናግረዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ባይሳ በዳዳ በበኩላቸው በቴክኖሎጂ ዘርፍ የፈጠራ ውጤቶች እንዲበራከቱ የሕግና የፖሊሲ ማሻሻያዎች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። የቡራዩ ተሰጥዖ ማበልፀጊያም የዚሁ ሥራ አንዱ አካል መሆኑን ገልጸው ማዕከሉ ወጣቶች አዳዲስ ኃሳብ እንዲያወጡ ተሰጥኦ ከኢትዮጵያ እንዳይወጣ ታስቦ መገንባቱን ተናግረዋል። በቀጣይም መሰል ተቋማትን ወደ ክልሎች ለማስፋት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሃሰን ሁሴን በበኩላቸው በማዕከሉ ቆይታ የሚያደርጉ ሥራ ፈጣሪዎች ሥልጠናውን በአግባቡ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ተናግረዋል።          
ተማሪዎችና መምህራን የተሳተፉበት ክልል አቀፍ  የሳይንስ ፈጠራ አውደ ርዕይ በባህርዳር ተከፈተ
Jun 3, 2023 85
ባህርዳር ግንቦት 26 /2015 (ኢዜአ)፡- በባህርዳር ከተማ ተማሪዎችና መምህራን የተሳተፉበት ክልል አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ ዛሬ ተከፈተ። በአውደ ርዕዩ ላይ የቀረቡት የፈጠራ ስራዎች ተወዳድረው ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ለሚወጡ የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተመልክቷል። አውደ ርዕዩ ለ4 ቀናት የሚቆይ መሆኑም ተገልጿል። ተወዳዳሪዎቹ ከሁሉም የክልሉ ዞኖች ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 142 ተማሪዎችና መምህራን ይዘው የቀረቡትን የፈጠራ ስራ በ5 ቡድን ተከፍለው መሆኑ ተገልጿል።   የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ማተብ ታፈረ በአውደ ርዕዩ መክፈቻ ላይ እንዳመለከቱት፤ ከድህነት ለመውጣት የሚያግዙ የፈጠራ ባለራዕይ ተማሪዎችንና መምህራንን ለማበረታታት በትኩረት ይሰራል። የፈጠራ አውደ ርዕዩን በመጎብኘት የፈጠራ ባለቤቶችን ማበረታታት ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል። ቢሮውም የፈጠራ ባለራዕዮችን በመደገፍና በማበረታታት በአውደ ርዕዩ ተወዳድረው አሸናፊ ለሚሆኑ ተማሪዎችና መምህራን በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ክልሉን ወክለው እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል። የክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽነር ዶክተር ሳሌ አያሌው በበኩላቸው፤ ተማሪዎችና መምህራን ለውድድር ይዘዋቸው የቀረቡት የፈጠራ ስራ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። የቴክኖሎጂ ፈጠራቸውን በአዕምራዊ ንብረት እንዲመዘገቡ ኮሚሽኑ እገዛ ያደርጋል ያሉት ዶክተር ሳሌ፤ ውጤታማ የሆኑትን የድካማቸውን ፍሬ እንዲያገኙ ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።   ነዳጅ አልባ ባጃጅ በፀሓይ ሃይል /ሶላር/ የሚሰራና ከወዳደቁ ብረቶች ሰርቶ በአውደ ርዕዩ ለውድድር ይዞ መቅረቡን የተናገረው ከምስራቅ ጎጃም ዞን ሸበል በረንታ ወረዳ የበረንታ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ጌታቸው አባተ ነው። ሁለት ሰው እንድትይዝ አድርጎ በሰራት ባጃጅም ዘወትር ከቤቱ ወደ ትምህርት ቤት፣ ከትምህርት ቤት ወደ ቤቱ ለትራንስፖርት እየተገለገለባት መሆኑን አስረድቷል። በቀጣይ አጋዥ አካል ባገኝ የትራንስፖርት ችግሩን ለማቃለልና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለማቃለል በብዛት አምርቼ ወደ ገበያ በማቅረብ ራሴንና ሀገሬን ለመጥቀም ራዕይ አለኝ ብሏል። ከአዊ ዞን ጓንጓ ወረዳ የስጋዲ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፊዚክስ መምህር መለሰ ግርማ በበኩላቸው፤ በአውደ ርዕዩ ለውድድር ይዞው የቀረቡት ዘመናዊ የእህል ማበጠሪያ ማሽን መሆኑን ገልጸዋል። "ሳድግ እናቴ ጤፍ ለማበጠር ሁልጊዜ ስትቸገር አይ ስለነበር ይህንን ሊያቃልል የሚችል ዘመናዊ የእህል ማበጠሪያ ማሽን ለመስራት አነሳስቶኛል " ብለዋል። በውድድሩም ከየምድቡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ለሚወጡ የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ከትምህርት ቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።      
አቶ ሰለሞን ሶካ በሞሮኮ በተዘጋጀው በጂኣይቴክስ አውደ ርዕይ ኢትዮጵያን ወክለው የተገኙ ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎችን ጎበኙ
Jun 3, 2023 102
አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ሰለሞን ሶካ በሞሮኮ በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ ('ጂ ኣይ ቴክስ') ኢትዮጵያን ወክለው የተገኙ ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎችን ጎብኝተዋል። በሞሮኮ ማራካሽ በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደዉ ኮንፍረንስ ላይ የአቅም ግንባታ ስራ ለሙያዊ ልህቀትና ኢኮኖሚ ልማት በሚል በተዘጋጀው መድረክ ላይ የተካፈሉት የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያውያን ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎችን መጎብኘታቸው ተገልጿል። በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው እና ትኩረቱን በሳይበር ደህንነት፣ በክላውድ ኮምፒውቲንግ ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በፊንቴክ (fintech)፣ በዲጂታል ከተማ፣ አግሪ ቴክ (agritech) መሰል የቴክኖሎጂ ዘርፎች ባደረገው ኮንፍረንስ ላይ ኢትዮጵያ ምርትና አገልግሎቶቿን አስተዋውቃለች። በጉብኝቱ ወቅት በሳይበርና መሰል ጉዳዮች ላይ አቅም ያላቸው አካላት ከኢመደአ ጋር በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባና ተቋሙ ለዚህ ዝግጁ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። በጉብኝቱ የኢመደአ ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶክተር) ተሳትፈዋል።
ስፖርት
በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን በ10 ሺህ ሜትር የሚወክሉ አትሌቶች የማጣሪያ ውድድር በስፔን ሊካሄድ ነው
Jun 5, 2023 49
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን በ10 ሺህ ሜትር የሚወክሉ አትሌቶች ማጣሪያ ውድድሩን በስፔን ማላጋ ከተማ እንደሚያካሂድ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ገለጸ። 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሀንጋሪ ቡዳፔስት በያዝነው ዓመት ነሐሴ ወር ውስጥ ይካሄዳል። በዚህ ውድድር ተሳታፊ ከሚሆኑ የተለያዩ አገራት አትሌቶች መካከል ለከፍተኛ ውጤት ከሚጠበቁት ውስጥ ኢትዮጵያዊን አትሌቶች ይገኙበታል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ውጤታማ ለመሆኑ የተለያዩ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል። የፌዴሬሽን ጽህፈት ቤት ተወካይ ዮሐንስ እንግዳ ለኢዜአ እንደገለጹት ለሻምፒዮናው አገራቸውን የሚወክሉ አትሌቶች መምረጥና ማዘጋጀት ከዝግጅቶች መካከል አንዱ መሆኑን ነው። የአትሌቶች ምርጫ የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕግና አሰራር በሚቅደው መሰረትና በፌዴሬሽኑ መመሪያና ደንብና መሰረት እንደሚከናወን ገልጸዋል። የዓለም አትሌቲክስ በዚህ ዓመት በ10 ሺህ ሜትር የሚካፈሉ አትሌቶች የሰዓት ማሟያ (ሚኒማ) ከሌላው ጊዜ በተለየ ከፍ እንደተደረገ ገልጸዋል። በ10 ሺህ ሜትር ኢትዮጵያን የሚወክሉ የአትሌቶች ሚኒማ ምርጫ በሃዋሳ ላይ ለማካሄድ እቅድ የነበረ ቢሆንም አትሌቶች ሰዓቱን ለማምጣት ስለሚቸገሩ የቦታ ለውጥ መደረጉን ተናግረዋል። ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት የአትሌቶች የሰዓት ማሟያ የማጣሪያ ውድድር በስፔን አገር ማላጋ ከተማ እንደሚካሄድ ነው የገለጹት። ከዚህ በፊት ይህን የማጣሪያ ውድድር በኔዘርላንድስ ሄንጌሎ ላይ ይደረግ እንደነበርም አስታውሰው በዚህ ዓመት ግን ውድድሩን ለማካሄድ ፍቃድ እንዳላገኙ እና በዚህ ምክንያት በስፔን የማጣሪያ ውድድሩ እንደሚካሄድ ተናግረዋል። በማራቶን ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችም በዚህ ሳምንት ውስጥ ይፋ እንደሚደረጉ ነው የገለጹት። በሌሎች ርቀቶች ላይ አገራቸውን የሚወክሉ አትሌቶች ምርጫ በተለያየ ውድድሮች ባስመዘገቡት ውጤት መሰረት እንደሚመረጡ አቶ ዮሐንስ አመልክተዋል።        
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በስዊድን ስቶክሆልም ማራቶን በሁለቱም ጾታዎች አሸንፈዋል 
Jun 5, 2023 67
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በስዊድን ስቶክሆልም ማራቶን ውድድር በሁለቱም ጾታዎች ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ በመያዝ በበላይነት ጨርሰዋል። በሳምንቱ መጨረሻ በተለያዩ አገራት የአትሌቲክስ ውድድሮች ተካሄደዋል። በሳምንቱ ከተደረጉ ውድድሮች መካከል በስዊድን የተካሄደው የስቶኮልም ማራቶን ይገኝበታል። በዚህ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል። በወንዶች አትሌት አሸናፊ ሞገስ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ አትሌት ደራራ ሁሬሳ ሁለተኛ እንዲሁም አትሌት ጸጋዬ መኮንን ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።   በሴቶቹ ውድድር አትሌት ሲፋን መላኩ አሸንፋለች። አትሌት ሶሮሜ ነጋሽ ሁለተኛ ሆና ስትጭርስ አትሌት የኔነሽ ዲንቄሳ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በስፔን አልባሴቴ የግማሽ ማራቶን ውድድር በሴቶች አትሌት ካሳነሽ ባዜ አሸናፊ ሆናለች። በደቡብ አፍሪካ በተደረገው የኔልሰን ማንዴላ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት በቀለች ወሬዮ ሶስተኛ ወጥታለች። አትሌት ሰላም ገብሬና ትዕግስት አያሌው በቅደም ተከተል አራተኛ እና አምስተኛ ደረጃን ይዘው ጨርሰዋል።
11ኛው የአማራ ክልል መስሪያ ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር በደሴ ከተማ ተጀመረ
Jun 4, 2023 69
ደሴ ግንቦት 27/2015(ኢዜአ)፡-ህብረተሰቡ በስፖርት የእርስ በእርስ ግንኙነቱን በማጠናከር ለአገር ሰላምና አንድነት በጋራ መስራት እንዳለበት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት ገለጹ። 11ኛው የአማራ ክልል መስሪያ ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር ዛሬ በደሴ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ውድድሩን ያስጀመሩት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት እንደገለጹት ስፖርት ጤናማ፣ ብቁና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ጉልህ ሚና አለው። በመሆኑም ህብረተሰቡ አንድነቱን ከመጠበቅ ባለፈ በስፖርት የእርስ በእርስ ግንኙነቱን በማጠናከር ለአገር ሰላም በጋራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ውድድሩ የመንግስት ሠራተኛውን ጤና ከመጠበቅ ባለፈ በየተሰማራበት የሙያ ዘርፍ ለህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ መነቃቃትን እንደሚፈጥርም ገልጸዋል። ከስምንት በላይ ክልሎች የሚሳተፉበት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የመንግስት ሠራተኞች ስፖርታዊ ውድድርም ከሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በደሴ ከተማ እንደሚካሄድና ለእዚህም ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የአማራ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ እርዚቅ ኢሳ በበኩላቸው፣ "በክልሉ ሠራተኞችን በስፖርት ውድድር በማሳተፍ ለህብረተሰቡ ፈጣንና የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ እየተሰራ ነው" ብለዋል። ስፖርት አካላዊ ብቃትንና ጤንነትን ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ሁሉም በየአካባቢው ስፖርትን ማዘውተር እንዳለበት መክረዋል። ዛሬ የተጀመረው የስፖርት ውድድር እስከ ሰኔ 7 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ እንደሚዘልቅ የገለጹት ኃላፊው፣ "በውድድሩም ከሁሉም የክልሉ ዞኖች የተውጣጡ ከ800 በላይ ሠራተኞች ይሳተፋሉ" ብለዋል።   እንደሃላፊው ገለጻ፣ ውድድሩ እግር ኳስንና መረብ ኳስን ጨምሮ በ5 የስፖርት ዓይነቶች ነው እየተካሄደ ያለው። ዓላማውም ጤናማና አምራች ሠራተኛ መፍጠር፣ የእርስ በእርስ ግንኙነትን ማጠናከርና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚካሄደው የመስሪያ ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር ክልሉን የሚወክሉ ስፖርተኞችን መምረጥ መሆኑን አቶ እርዚቅ አስረድተዋል። ባህር ዳር ከተማን ወክለው በእግር ኳስ ከሚሳተፉ ሠራተኞች መካከል አቶ ሀይለየሱስ ሙሉዓለም በበኩላቸው "በውድድሩ ጤናችንን ከመጠበቅና ግንኙነታችንን ከማጠናከር ባለፈ ሰላማችንን እንጠብቃለን" ብለዋል። "በእግር ኳስ ውድድር አሸናፊ በመሆን ክልሉን ለመወከል ቅድመ ዝግጅት አድርገን ነው የመጣነው፤ ለማሸነፍ የምንችለውን ያህል እንጥራለን" ሲሉም ገልጸዋል። በውድድሩ ማስጀመሪያ ላይ ደሴ ከተማን የወከለው ወሎ ዩኒቨርሲቲ ባህር ዳር ከተማን ከወከለው ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በአግር ኳስ ጨዋታ ውድድር አካሂደዋል። በማስጀመሪያ ስነስርአቱ ላይም የፌዴራል የክልል፣ የደቡብ ወሎ እና የደሴ ከተማ ሥራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።      
አካባቢ ጥበቃ
በሶማሌ ክልል ለአካባቢ ጥበቃና ልማት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ መንግስት አስታወቀ
Jun 5, 2023 47
ጅግጅጋ ግንቦት 28 / 2015(ኢዜአ)፡- በሶማሌ ክልል የተፈጥሮ ሀብትን በመንከባከብ ለአካባቢ ጥበቃና ልማት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ መንግስት አስታወቀ። የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ቀን በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ካራማራ ተራራ ላይ ዛሬ ዕለቱን በተመለከተ ውይይትና በችግኝ ተከላ መረሃ ግብር ተከብሯል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ተወካይና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱላሂ አደን ዕለቱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት ፤ እንደ ማህበረሰብ አካባቢን መንከባከብና መጠበቅ ካልተቻለ ለቀጣይ ትውልድ አስቸጋሪ መልካምድር እየተፈጠረ መሆኑን መገንዘብ ይገባል ብለዋል። ሰዎች በደኖች ላይ በሚያደርሱት ጉዳት በሚፈጠረው በረሐማነት አርብቶና ከፊል አርብቶ አደሩ በዝናብ እጥረት ለተደጋጋሚ ድርቅ እየተጋለጠ ነው ያሉት አቶ አብዱላሂ፤ የክልሉ መንግስት ለአካባቢ ጥበቃና ልማት ልዩ ትከረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።   የሶማሌ ክልል አካባቢ ጥበቃና የገጠር መሬት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሁየዲን አብዲ በበኩላቸው፤ ቢሮው ከአካባቢ ጥበቃ ስራ ባሻገር በክልሉ ውስጥ በሚገኙ የዱር እንስሳት ጥበቃ ላይ ሰፊ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል። አለም አቀፉን የአካባቢ ጥበቃ ቀንን በካራማራ ተራራ ላይ መከበሩም የተራራውን ብዝሐ ህይወትና ታሪካዊ ሥፍራነቱን ለመጠበቅ ያግዛልም ብለዋል።   የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና ፕላስቲክ አወጋገድ ላይ ትልቅ ክፍተት ያለበትና የከተማ ብክለት እያስከተሉ በመሆናቸው ለመከላከል ሁሉም ባለ ድርሻ አካል በቅንጅት መስራት እንዳለበት ያመለከቱት ደግሞ የጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ዚያድ አህመድ ናቸው። በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያም በጅግጅጋ ከተማ በደረቅ ቆሻሻ ማስወገድ ስራ ላይ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ማህበራት እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። "የፕላስቲክ ብክለት ተፅዕኖን እንግታ " በሚል መሪ ሀሳብ የተከበረው የአካባቢ ጥበቃ ቀን መርሃ ግብር ያዘጋጀው የክልሉ የአካባቢ ጥበቃና የገጠር መሬት አስተዳደር ቢሮ ነው። በመርሃ ግብሩ የክልሉ መንግስት ከፍተኛ አመራሮች፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች ፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።  
የጭሮ ከተማን ውብና ፅዱ ለማድረግ በ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ዘመናዊ የቆሻሻ ማስወገጃ ሊገነባ መሆኑ ተገለጸ
Jun 5, 2023 97
ጭሮ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)---በምዕራብ ሀረርጌ ዞን የጭሮ ከተማን ውብና ፅዱ ለማድረግ በ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ዘመናዊ የቆሻሻ ማስወገጃ ሊገነባ መሆኑን የከተማው አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በከተማው ለ50ኛ ጊዜ የተከበረውን የአለም አካባቢ ቀን በማስመልከት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ቆሻሻ አወጋገድ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል።   በዚሁ ጊዜ የተደራጀ የቆሻሻ ማስወገጃ ስፍራ መገንባትና ስርዓትን የተከተለ ቆሻሻ አወጋገድ እንዲኖር እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል። የጭሮ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሀመድ ኡመር፣ ጭሮ ከተማን ማራኪ ገፅታ ለማላበስ በየአካባቢው ቆሻሻ ስርዓት ባለው መልኩ እንዲወገድ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ''ጭሮን ውብ፣ ጽዱና ማራኪ ከተማ የማድረግ ግባችንን ለማሳካት የተደራጀ የቆሻሻ ማስወገጃ ሳይት ከማስገንባት በላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ መለወጥ ትልቁ ስራችን ነው'' ሲሉም ገልጸዋል። በተለይም በከተማው በስፋት ተጥሎ የሚገኘውን የፕላስቲክ መገልገያዎች አወጋገድን በተመለከተም ብዙ መሰራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የጭሮ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብሳ ኢብራሂም በበኩላቸው ጭሮን ውብና ፅዱ ከተማ የማድረግ እቅዱን ለማሳካት በ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ዘመናዊ ቆሻሻ ማስወገጃ ሊገነባ ነው ብለዋል። ፕሮጀክቱ ከተማዋን ለኑሮ ምቹና ዘመናዊ የማድረግ የመጀመሪያው እርምጃ መሆኑን ገልጸው ለተደራጀ ቆሻሻ አወጋገድ ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠትም ከቆሻሻ ማስወገጃ ግንባታ ጎን ለጎን ማህበረሰቡን ያሳተፈ ሳምንታዊ የአካባቢ ፅዳት ዘመቻ እያካሄዱ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡ ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ወይዘሮ ፋጡማ አወል ከተማዋን ፅዱና ውብ ለማድረግ ጽዳት ማከናወን ብቻ በቂ አለመሆኑን ጠቅሰው ለቆሻሻ አወጋገዱም ትኩረት መስጠት ይገባል ብለዋል። ከተማዋ በተለይ በወንዞች ዳርቻ የፕላስቲክ ኮዳዎች በስፋት እየተከማቸ በመሆኑ ወንዞችን ጽዱ በማድረግ የአካባቢ ብክለትን መከላከል እንደሚቻልም አንስተዋል። ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ሙስጠፋ ሳሊ በበኩላቸው ተስማሚ አየር ያለበት ፅዱ አካባቢን እውን ለማድረግ ሁሉም በየራሱ መንደር ተጨባጭ ስራ መስራት እንዳለበት አመልክተዋል። ሁላችንም ቆሻሻን በዘፈቀደ ከመጣል መቆጠብና ይህን በተላለፉ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ተጠያቂነት ማስፈን ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል።        
የፕላስቲክ ምርቶች ለአካባቢ ብክለት መንስዔነታቸው እየጨመረ ነው
Jun 5, 2023 54
አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ የፕላስቲክ ምርቶች ለአካባቢ ብክለት መንስዔነታቸው እየጨመረ በመምጣቱ ችግሩን ለማስወገድ ሕብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ጠየቀ፡፡ ባለሥልጣኑ የዓለም የአካባቢ ቀንን ምክንያት በማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ ከ400 ሚሊየን ቶን ፕላስቲክ የሚመረት ሲሆን፤ ከዚህም ውስጥ ግማሽ የሚሆኑት ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ መሆናቸውን መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ በኢትዮጵያም የፕላስቲክ ምርቶች ለአካባቢ ብክለት መንስዔ እየሆኑ መምጣታቸው ይነገራል።   ለአብነትም በየዓመቱ ከ900 ሺህ ቶን በላይ አዳዲስ የፕላስቲክ ማሸጊያዎች ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ሲሆን፤ ከዚህም ውስጥ መልሶ ጥቅም ላይ የሚውለው ከ5 በመቶ እንደማይበልጥ መረጃዎች ያሳያሉ። የአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ ዶክተር እሸቱ ለማ እንዳሉት፤ የፕላስቲክ ምርቶች በከተማው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ እና በአካባቢ ብሎም በእንስሳት ላይ ጭምር አደጋ እያስከተለ ነው። በከተማው ጥቅም ላይ እየዋሉ ያሉ አብዛኛው የፕላስቲክ ምርቶች የአገልግሎት ዘመናቸው አጭር ጊዜ ወይም ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል ነው። በዚህም ሳቢያ የቆሻሻ ምርት መጠን እንዲጨምር እያደረገ መሆኑንም አብራርተዋል። በመሆኑ ኤጀንሲው ብክለቱን ለመቀነስ እየሰራ ሲሆን፤ ሕብረተሰቡ በተለይ የፕላስቲክ ምርቶች አወጋገድ ላይ እየተሰራ ያለውን ሥራ እንዲያግዝ ጠይቀዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ሥራ አስኪያጅ ዲዳ ድሪባ በበኩላቸው፤ ዜጎች እፅዋትን በመትከልና በመንከባከብ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትላቸውን አደጋዎች ለመቀነስ ርብርብ መደረግ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ ስነ-ምህዳርን በመጠበቅ፣ ብክለትን መከላከል፣ ካርቦን ልቀትን መቀነስና ወደ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ እና ማቃጠያዎች የሚላከውን የቆሻሻ መጠን መቀነስ ይገባል ነው ያሉት፡፡ የውይይቱ ዓላማም የአካባቢ ብክለትን ሊፈጥሩ የሚችሉ ቁሳቁሶችን በግለሰብ ደረጃ በአግባቡ በማስወገድና ወንዞችን ከብክለት መጠበቅ እንዲቻል ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።                      
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በአገሪቱ ሁለንተናዊ ልማት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ ይቀጥላል - ፕሬዝዳንቱ
Jun 5, 2023 39
ባህር ዳር ግንቦት 28/2015(ኢዜአ) የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ60 ዓመታት ጉዞው የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት በአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ያበረከተውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ፍሬው ተገኘ ገለጹ። ዩኒቨርሲቲው 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የመዝጊያ ሥነ ሥርዓትና የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀንን አስመልክቶ በቤዛዊት ተራራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ዛሬ አካሂዷል።   የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ፍሬው ተገኘ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው ባለፉት ስድስት አሥርት አመታት ለአገሪቷ የሰው ኃይል በማሰልጠን፣ በጥናትና ምርምርና ማሀበረሰብ አገልግሎት ያበረከተውን አስተዋጽኦ ወደፊትም አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ልዩነት የሚፈጥሩና የኅብረተሰቡን ችግሮች የሚፈቱ ሳይንሳዊ ምርምሮች ላይ በማተኮር በአፍሪካ ምርጥ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ለመሆን የያዘውን ራዕይ ለማሳካት እንደሚሰራም አስታውቀዋል። ዩኒቨርሲቲው የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በምርምር የተደገፉ ተግባራት ከማከናወን ባለፈ፤ የአካባቢ ጥበቃ ሥራን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም አመልክተዋል። መንግሥት ይፋ ያደረገውን የበጋ መስኖ የስንዴ ልማት ውጤታማ ለማድረግም አርሶ አደሩን በግብዓት የመደገፍ፣የማማከርና የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑንም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። የምስረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግም በባህር ዳር ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ከባለሃብቶች ጋር ተባብሮ በማስገንባት አሻራውን በማሳረፍ ላይ ነው ብለዋል። ከፕሮጀክቶቹም የባህር ዳር አብርሆት ቤተ መጻህፍት፣ ልዩ ትምህርት ቤትና የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች እንደሚገኙበት ዶክተር ፍሬው አስታውቀዋል። በቤዛዊት ተራራ የተከናወነው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብርም ዩኒቨርሲቲው ለሥነ-ህይወታዊ ሥራ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን አስረድተዋል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኃይለማርያም ከፍያለው በበኩላቸው አረንጓዴ ልማት ለሰብል፣ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና የአካባቢን ሥነ-ምህዳር ለመጠበቅ ዓይነተኛ መፍትሄ መሆኑን አመልክተዋል። የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲም ትውልድን በእውቀትና በአመለካከት ከመቅረጽ ባሻገር፤ የኢኮኖሚ መሠረት የሆነውን የአካባቢ ሥነ-ምህዳር በመጠበቅ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል። የአካባቢ ሥነ-ምህዳርን ከሚያስጠብቁ ሥራዎች መካከል ሥነ-ህይወታዊ ሥራዎችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ መተግበር እንደሚኖርባቸው አስረድተው፤ ለዚህም ዩኒቨርሲቲው አካታች የሆነ ሥነ-ህይወታዊ ሥራ በመስራት አርአያነት ያለው ተግባር እያከናወነ ነው ብለዋል። በተለይም በክልሉ አምስተኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ፈጥኖ በመጀመሩ ሌላውን ህብረተሰብ የማነሳሳት ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸው፤ ቢሮውም ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ለሚያከናውናቸው ሥራዎች ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በአማራ ክልል ለአምስተኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ከቢሮው የተገኘ መረጃ ያስረዳል። በችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩ ላይ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲና የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አመራሮች ተገኝተዋል።    
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ፕሬዝዳንት ፑቲን ለአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
May 25, 2023 272
አዲስ አበባ ግንቦት 17/2015 (ኢዜአ)፦የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን ለቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለአሁኑ የአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንከዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት ለአፍሪካውያን የድል ምልክት ነው ያሉ ሲሆን የአፍሪካውያን የነጻነት፣የሰላምና የብልጽግና ፍላጎት ማሳያ ነው ብለዋል። ህብረቱ ከተመሰረተበት ግዜ አንስቶ ለብዙ አስርተ ዓመታት በዓለም አቀፍ መድረኮች አፍሪካውያንን በመወከል የባለብዙ ወገን ውይይቶችንና ትብብርን በማጎልበት ትልቅ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት ለችግሮቻቸው በጋራ ምላሽ የሚሰጡበትን መንግድ ያመቻቸ መሆኑን ጠቁመው አህጉራዊ ትብብርን በተለያዩ መስኮች እንዲያጠናከሩም መንገድ ከፍቷል ብለዋል። በዚህም ለአፍሪካ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት የላቀ ሚና ማበርከቱንና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ያላትን ተሳትፎ እንድታሳድግ ህብረቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ሩሲያ ከአፍሪካ አጋሮቿ ጋር ያላትን ወዳጅነት ለማጠናከር ልዩ ትኩረት ትሰጣለች ያሉት ፕሬዝዳንቱ እ.አ.አ በ2019 የተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ -ሩሲያ ጉባኤ በአፍሪካና በሩሲያ መካከል ያሉ ትብብሮች እንዲጠናከሩ አስችሏል ብለዋል። በመጪው ሃምሌ ወር በሩሲያ የሚካሄደው ሁለተኛ የአፍሪካ ሩሲያ ጉባኤም ሩሲያ ከአፍሪካ ጋር ለሚኖራት ትብብር አዲስ ምዕራፍ እንደሚፈጥር ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 4242
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተገለጸ
Dec 20, 2022 1688
አዲስ አበባ ታኅሳስ 11/2015 (ኢዜአ) አህጉራዊው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና አፍሪካ ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ግንኙነትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተመላከተ። የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ከአፍሪካ ጋር ያላት የንግድ ትስስር ከባህረ-ሰላጤው ሃገራት መካከል በቀዳሚነት እንደሚጠቀስም ተገልጿል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዊሊያም ስቴንሀውስ ከሲ ጂ ቲ ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በተለይም ዱባይ የአፍሪካን ንግድና ኢንቨስትመንት በተመለከተ ዋና ማዕከል ሆናለች ብለዋል። በዱባይ 25ሺህ ገደማ የአፍሪካ ካምፓኒዎች እንደሚንቀሳቀሱ አመልክተው ይህም ሀገሪቱ በነጻ የንግድ ቀጣናው የቢዝነስ አጋር እንድትሆን አስችሏታል ነው ያሉት። አፍሪካውያን ባለሃብቶች የግብይት ማዕከላቸውን በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በማድረግና ምርቶችን ወደ አህጉሪቷ በማስገባት በነጻ ንግድ ቀጣናው ስር የገልፍ ሀገራትን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደጉት እንደሚገኝም አስገንዝበዋል። የዱባይ ወደብ በአፍሪካ ያለው ተደራሽነት መስፋፋትም አፍሪካ ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ጋር የሚኖራትን የሎጀስቲክስ አቅርቦት እንደሚያሳድግ በመረጃው ተመላክቷል። ከገልፍ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት ከኢኮኖሚያዊ ትስስር ባለፈ ዲፕሎማሲያዊና ወንድማማችነትን መሠረት ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤሜሬት የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ ናቸው። አምባሳደሩ እንደሚሉት ከመካከለኛው ምስራቅ መነሻቸውን ያደረጉ ባለሃብቶችና የቢዝነስ ሰዎች ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጋር በልዩ ልዩ ዘርፎች ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ይገኛል። እ.አ.አ በጥር 2021 ተግባራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ከአጀንዳ 2063 ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የአህጉሪቱን ወሳኝ የኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም የዲጂታል ንግድ፣ የኢንቨስትመንት ትስስርና ሌሎች የንግድ ግንኙነቶችን በነጻ የንግድ ቀጣና ለማከናውን የተካሄደ ስምምነት ነው።
ሐተታዎች
አፋጣኝ መፍትሔ የሚያሻው የምርታማነት ፀር
May 27, 2023 204
  (ኤልያስ ጅብሪል) አሲዳማ አፈር የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከሰባት በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al+3) ንጥረ- ነገሮች የሚበዙበት አፈር ማለት ነው፡፡ የአፈር አሲዳማነት በሀገራችን በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ የሚገኝ የአፈር ለምነት ችግር ሲሆን፤ ከፍተኛ ዝናብ የሚያገኙና በምርታማነታቸው የተሻሉ ናቸው የሚባሉትን የሀገሪቱን አካባቢዎች ጭምር እየጎዳ መሆኑንም ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት፡፡ የአፈር ጤንነት ችግሮች በሦስት ዋና ዋና መንገዶች ይገለፃሉ፡፡ ይኸውም አሲዳማነት፣ የጨዋማነት ችግር የሚነሳበትና ኮትቻማ/ጥቁር ወይም መረሬ አፈር/ ብሎ ማስቀመጥ እንደሚቻል በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊ ፋኖሴ መኮንን ይናገራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ከ15 ሚሊየን ሄክታር በላይ የሚታረስ መሬት ሲኖር ወደ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በአሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነ ነው የጠቀሱት፡፡ አፈር ሰብሎች የሚፈልጓቸውን ንጥረ-ነገሮች በተሟላና በተመጣጠነ መልኩ ሳይዝ ሲቀር ምርታማነት ጥያቄ ውስጥ እንደሚወድቅ አቶ ፋኖሴ ይገልጻሉ። ከዚህ አኳያ በኢትዮጵያ ከ1 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጎዳ በመሆኑ ምርታማነቱ ምንም በሚባል ደረጃ የሚቀመጥ መሆኑን ይጠቁማሉ። እፅዋት ከአየር፣ ውሃና የፀሐይ ብርሃን በተጨማሪ 18 ዓይነት ንጥረ-ነገሮችን ከአፈር ውስጥ ሊያገኙ እንደሚችሉ ነው ኃላፊው የገለጹት፡፡ የአፈር አሲዳማነት መንስኤዎች አሲዳማነት በአንድ ጊዜ ተፈጥሮ የሚቆይ ሳይሆን በሂደት እየጨመረ እና እየተስፋፋ የሚሄድ ክስተት ነው፡፡ ለአፈር አሲዳማነት በዋነኝነት የዝናብ መብዛት፣ የአፈር መሸርሸር፣ የሰብል ተረፈ-ምርት ሙሉ በሙሉ ከማሳ ማንሳት እና ፍግ አለመጠቀም፣ እንዲሁም አሲዳማ ዝናብ የመሳሰሉት አፈር ውስጥ ያሉ ለተክሉ እድገት ጠቃሚ ንጥረ-ነገሮች እንዲሟጠጡ እንደሚያደርግ በመንስኤነት ይጠቀሳሉ። የአፈር አሲዳማነት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚስተዋል ሲሆን ለአብነትም አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ተጠቃሾች እንደሆኑ አቶ ፋኖሴ ተናግረዋል፡፡ አሲዳማ አፈርን በኖራ የማከም ዘዴ አሲዳማ አፈርን ለመከላከል በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ መንገዶች ከሚወሰዱ እርምጃዎች ባሻገር አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ በዋናነት የሚጠቀስ መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ አፅንዖት ሰጥተው የተናገሩት፡፡ የተለያዩ አፈርን የማከሚያ ግብአቶች ያሉ ቢሆንም በቀላሉ ከመገኘትና ከዋጋው ርካሽነት አንፃር ካልሽየም ካርቦኔት ወይም “ የግብርና ኖራ" እየተባለ የሚጠራው በስፋት አገልግሎት ላይ እንደሚውል ገልጸዋል፡፡ ወደ 15 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር የሚታረስ መሬት ሲኖር፤ ከዚህ ውስጥ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር ወይም ከ43 በመቶ የማያንሰው በአሲዳማ አፈር የተጠቃ መሆኑን ጠቅሰው፤ ወደ 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነው በጠንካራ አሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነና በኖራ መታከም ያለበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ጠንካራ አሲዳማ አፈር ስንል የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከ 5 ነጥብ 5 በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al3+) ካታየኖች የሚበዙበት አፈር ሲሆን፤ የእነዚህ ካታየኖች መብዛት የሰብሎችን ሥር በመመረዝ በዕድገታቸው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን እንደሚፈጥር ነው ከግብርና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ የሚጠቁመው፡፡ ፒ ኤች መጠኑ ከሰባት ወደ ዜሮ እየቀነሰ ሲሄድ የአሲድነቱ ጥንካሬ የሚጨምር ሲሆን ከሰባት ወደ 14 ሲጨምር የጨዋማነቱ ባህሪ እንደሚጨምር ነው የዘርፉ ባለሙያዎች የሚያስቀምጡት። በአገራችን ሁኔታ አሲዳማ አፈርን ለማከም ኖራ መጠቀም የሚያስፈልገው የአፈሩ ፒ ኤች መጠን ከ5 ነጥብ 5 በታች ሲሆን ነዉ፡፡ ኖራ በተፈጥሮ የሚገኝ የካልሲየም እና የማግኒዚየም ካርቦኔት ሃይድሮኦክሳይድ ውህድ ሲሆን፤ አሲዳማ አፈር ውስጥ በሚጨመርበት ወቅት አሲዳማ አፈር ውስጥ የሚገኙትን አልሙኒየም እና ሃይድሮጂን አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን በመግታት የአፈሩን ፒ ኤች መጠን ከፍ በማድረግ ለእፅዋት እድገት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ በአማካይ በአፈር አሲዳማነት የተጎዳ መሬትን ለማከም በሄክታር 30 ኩንታል የግብርና ኖራ እንደሚያስፈልግ ባለሙያዎች ይመክራሉ። በአሲዳማነት የተጠቃ መሬት አሲዳማነትን የሚቋቋሙ ሰብሎች ካልተዘሩበት ወይም አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ ካልተሰራ የሚሰጠውን የአፈር ማዳበሪያ ከጥቅም ውጭ በማድረግ ለኪሳራ ይዳርገናል ነው ያሉት፡፡ እንደ አኩሪ አተር፣ ካሳቫ፣ አናናስ፣ ዳጉሳ፣ ቡና፣ ሻይ እንዲሁም የስንዴ ዝርያዎች አሲድን የመቋቋም ባህሪ እንዳላቸውም ተመላክቷል፡፡ ግብርና ሚኒስቴር በአሲዳማነት ከተጠቃው 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነውን በአሥር ዓመት ውስጥ ለማከም ዕቅድ የያዘ ቢሆንም በዕቅዱ መሰረት በዓመት 400 ሺህ ሄክታር መሬት ለማከም ወደ 5 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት፡፡ ከበጀት አንጻር ይህን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በየዓመቱ ከመንግሥት ካዝና ማግኘት ከባድ በመሆኑ ከእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች፣ ከአጋር አካላት ድጋፍ ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን ነው ያስታወቁት። ምንም እንኳን በአሲዳማነት የተጠቃውን አፈር ማከም ወጪው ከፍተኛ ቢሆንም አፈሩ ሳይታከም በቆየ ቁጥር ከምርት ውጭ የመሆን ዕድሉ እየጨመረ ስለሚሄድ አገርን የሚያሳጣው ዋጋ ከፍተኛ እንደሚሆን በውል መረዳት ያሻል። በዚህም የአፈር አሲዳማነት ጉዳይ መፍትሔ ካልተሰጠው ምርታማነትን ከ50 በመቶ እስከ 100 በመቶ ሊያሳጣ እንደሚችል ነው በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊው ፋኖሴ መኮንን የሚናገሩት፡፡ ከአፈር አሲዳማነት የተነሳ በየዓመቱ ወደ 9 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በኢትዮጵያ ደረጃ በስንዴ ከሚሸፈነው መሬት ብቻ እየታጣ እንደሆነ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ይህ በስንዴ ብቻ ከሚሸፈን መሬት የተወሰደ ግምት ሲሆን በገብስ፣ ጤፍ ወዘተ… ቢታሰብ ምን ያህል የምርት ማሽቆልቆል እንደሚያስከትል ማወቅ ይቻላል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ የስንዴ ምርት በአማካይ በሄክታር እስከ 40 ኩንታል ምርት ሊሰጥ ይችላል፤ ሆኖም ግን የአፈር ጤንነቱን በመጠበቅ አስፈላጊውን ግብአት የምንጠቀም ከሆነ በሄክታር 60 ኩንታል በማምረት አገራችን የጀመረችውን ምርትና ምርታማነትን የማረጋገጥ ሥራ ማከናወን ያስችለናል ነው ያሉት፡፡ ይህንንም ከግብ ለማድረስ የግብርና ሚኒስቴር የመጀመሪያው የትኩረት አቅጣጫው የአሲዳማ አፈር ልማት መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ ያስረዱት፡፡ አሲዳማ አፈሩን ለመከላከል በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ባለፉት ሦስት ዓመታት 38ሺህ 369 ሄክታር መሬት በኖራ የማከም ሥራ መከናወኑ ተገልጿል። ይህ ከሚኒስቴሩ ዕቅድ አኳያ ሲታይ በጣም ዝቅተኛ አፈጻጸም ነው። የአፈር አሲዳማነትን ለማከም የግብርና ኖራ ምርት ላይ የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች አቅርቦቱን በሚፈለገው ደረጃ ቢያቀርቡም፤ የኖራ ምርቱ በብዛት ያለበት ቦታ እና አሲዳማ መሬቱ የሚገኝበት ርቀት በተቃራኒው በመሆኑ ከትራንስፖርት አንጻር ያለው ችግር ሥራውን አድካሚ እንዳደረገው ነው የሚኒስቴሩ መረጃ የሚያመለክተው። ነገር ግን አርሶ አደሩ አንድ ጊዜ መሬቱን በኖራ ማከም ከቻለ እስከ አምስት ዓመት ሊያገለግለው ይችላል። ከዚያም በኃላ ቢሆን የተወሰነ የምርት መቀነስ እንጂ በምርታማነት ላይ የጎላ ችግር አይኖረውም ነው ያሉት። ስለሆነም ኖራን የመጠቀም ሁኔታ አቅም ያለው አርሶ አደር በግዥ መልክ እንዲጠቀም፤ አቅም የሌለው ደግሞ መንግሥት ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል። እንደ ምዕራብ ኦሮሚያ ነጁ፣ መንዲ፣ ምዕራብ ወለጋ እንዲሁም በአማራ ክልል አዊ ዞን፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አብዛኛውን ወረዳዎች በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጠቁ በመሆናቸው ምርት ለመስጠት የማይችሉበት ደረጃ ላይ እየደረሱ መሆኑን አቶ ፋኖሴ ገልጸዋል። ዝዋይ፣ ሐዋሳ፣ መራቤቴ፣ ደጀን፣ ጉደርና የመሳሰሉት በመንግሥትም ሆነ በግል የግብርና ኖራ ምርት የሚቀርብባቸው ቦታዎች መሆናቸው ነው የተጠቆመው። በእነዚህ ቦታዎች የምርትና የጥሬ ዕቃ ችግር የሌለና የግብርና ኖራ ዋጋም በኩንታል እስከ 350 ብር እየተሸጠ ነው ብለዋል። የአፈር አሲዳማነት በረዥም ጊዜ የተፈጥሮ መዛባት ሂደት ውስጥ የሚከሰት እንደመሆኑ መጠን አንዴ ችግሩ ከተከሰተ በኋላ መፍትሔ በመስጠት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ወጪ እና ርብርብ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም ችግሩ ከመከሰቱ በፊት የአፈር አሲዳማነትን ለመከላከል የሚያስችሉ እርምጃዎችን መውሰድ ተገቢነት ያለው ጉዳይ እንደሆነ ነው የተጠቆመው፡፡ መንግሥት በያዘው የሌማት ትሩፋትና የግብርና ኢኮኖሚ አቅጣጫ በተለይም የስንዴ ምርት ከራስ ፍጆታ አልፎ ለሌሎች አገራት ምርቱን በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት በሚደረገው ጥረት የአፈር ምርታማነትን/ጤንነቱን መጠበቅ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑ የግድ ነው። “ለም አፈር በሌለበት ምርትና ምርታማነት የማይታሰብ ነው” የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ ግብርና የመሪነት ተግባሩን እንዲወጣ በቅድሚያ የአፈር ጤንነት ሊጠበቅ ይገባል ብለዋል። በመሆኑም ከዚህ በፊት ያለውን የግንዛቤ ችግርና ከአመራሩ እስከ አርሶ አደሩ ያለውን ክፍተት በመቅረፍ ችግሩን ለመቀነስ እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል። ሁሉንም ነገር ከመንግሥት መጠበቅ የለብንም የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ በቅድመ-መከላከል ሥራ ችግኝ በመትከል፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ በማከናወን፣ በተፈጥሮ ማዳበሪያ (ኮምፖስት) የራስን ማሳ በመንከባከብ፣ አማራጭ ሰብሎችን እያፈራረቁ በመዝራት፣ አሲዳማነትን መቋቋም የሚችሉ ተክሎችን በመምረጥ ማልማት እንዲሁም የግብርና ኖራ በመጠቀም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አብራርተዋል። በሀገራችን በተለያዩ የምርምር ተቋማት የተሰሩ ምርምሮች እንደሚያሳዩት አሲዳማ አፈርን ለማከም የተፈጥሮ ማዳበሪያዎችን ከኖራ ጋር አቀናጅቶ በመጠቀም በዋና ዋና ሰብሎች ላይ እስከ ሁለት እጥፍ የምርት ጭማሪ ማግኘት እንደሚቻል ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በመሆኑም አርሶ አደሮች ኖራ በግዥና በብድር የሚያገኙበትን ሥርዓት በተጠናከረ አግባብ መተግበር ያስፈልጋል። ልክ እንደ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በግዥ ወይም በብድር የግብርና ኖራ በማቅረብና በአሲዳማነት የተጎዳው መሬት እንዲያገግም ማድረግ ላይ አትኩሮ መስራት ሌላው የመፍትሄ አካል ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል። የእርሻ መሬት አያያዝና እንክብካቤ ጉዳይ የህግ ማዕቀፍ ኖሮት በዚያ አግባብ ተግባራዊ ማድረግም በተለይ በአሲዳማነት የመጠቃት አዝማሚያ የተጋረጠበትን የእርሻ መሬት ለመታደግና የተጎዳውንም እንዲያገግም ለማከም የሚሰሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ያስፈልገዋል። ከዚህ ባለፈም በአንድ የእርሻ ቦታ ላይ የተለያዩ ሰብሎችን መዝራት፣ አፈር ውስጥ ህይወት ያላቸው ነገሮች እንዲኖሩ ማድረግና የአፈሩን እርጥበታማነት ማዝለቅ ተገቢ ይሆናል።            
አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታና አብሮነት
May 3, 2023 989
በጣፋጩ ሰለሞን አገራችን ኢትዮጵያ የተለያየ ቋንቋ፣ ባህልና እምነት ያላቸው በርካታ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ተቻችለው፣ ተከባብረው፣ ተዋደው፣ በአንድነትና በአብሮነት በፍቅር የሚኖርባት አገር ነች። በዚህም የብሄር ብሄረሰቦች ሙዝዬም ነች የሚል አድናቆትን ተጎናፅፋለች-ኢትዮጵያ። እነዚህ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች የራሰቸው መገለጫ የሆኑ ቱባ ባህል አላቸው። ኢትዮጵያውያን ለዘመኑ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጥበብ መሰረት የሆኑ የአያሌ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤቶች ናቸው። ባህላዊ የመድኃኒት ቅመማና የህክምና ጥበብ ኢትዮጵያ ለዓለም ካበረከተቻቸው ትሩፋቶች መካከል አገር በቀል ዕውቀቶች ተጠቃሽ እንደሆኑ የታሪክ ድርሳናትና ሌሎች የየዘርፉ ተጓዳኝ መረጃዎች ያስረዳሉ። በተለይ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የተጠቀሙባቸውና እየተጠቀሙባቸው ያሉ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሌሎችም ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀሱ ናቸው። በጂንካ ዩኒቨርስቲ 5ኛው አገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ ሰሞኑን ተካሂዷል። በኮንፈረንሱ በአገር በቀል ግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም፣ለአብሮነት ትስስር እና ለአገራዊ ዕድገት ያላቸው ሚና የሚል እሳቤን ዓላማ ያደረገ ጥናት ቀርቧል። ጥናቱ እ.ኤ.አ ከ2018 እስከ 2022 ባሉ ዓመታት በመስቃን እና በማረቆ ህዝቦች ባህላዊ የግጭት አፈታት ላይ መሰረት አድርጎ የተካሄደ ነው። ጥናቱን ያካሄዱት "አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሰላም፣ ለፀጥታ እና ለዕድገት ያላቸው አስተዋፅኦ፤The Role of Indigenous conflict resolution Mechanism for peace,Security ,and Sustainable Development in Ethiopia " በሚል ርዕስ ያካሄዱት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ ዮሐንስ ተስፋዬ ናቸው። የጥናቱ ግኝት እንደሚያመለክተው ዘመናትን ተሻግረው እዚህ የደረሱ የሰላም ግንባታና ማጠናከሪያ የሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች አሁን ለደረስንበት ሳይንሳዊ ጥበብ መጎልበት እያገለገሉ ነው። የጥናት አቅራቢው ለኮንፈረንሱ ታዳሚዎች እንዳብራሩት ጥናቱ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ለአብሮነትና ለዕድገት አይተኬ ሚና አላቸው። እነዚህን አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች በአግባቡ መጠቀም ይገባል። እሳቸው እንዳብራሩት በአገራችን ሶስት አይነት የግጭት አፈታት ዘዴዎችን እንጠቀማለን። የወንጀልና የፍትሐብሔር ህጎች፣ እንደ ሽምግልና ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች እና ከሃይማኖታዊው ደግሞ ሸርዓ ከምንጠቀምባቸው የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ናቸው። ተመራማሪ ዮሐንስ እንዳሉት ጥናቱ በተካሄደበት በጉራጌ ዞን በመስቃን እና በማረቆ መካከል አጋጥሞ የነበረውን አለመግባባት ከመፍታት አኳያ ከዘመናዊ እውቀቶች ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ትልቅ ሚና ነበራቸው። በመስቃን እና በማረቆ ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት ከመስቃን፤ ከማረቆ እንዲሁም ከአጎራባች የኦሮሚያና ስልጤ ዞኖች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ተሳትፈዋል። በመስቃን እና በማረቆ መካከል ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት የተሳተፉት የሀይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች ግጭቱን ለመፍታት የተጠቀሙት ጥበብ አገር በቀል ዕውቀቶች በዘመናዊ ህግና አሰራር የማይቻሉትን የመፈጸምና ማህበራዊ አንድነትን ከማጠናከር አንፃር ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የጥናቱ ግኝት አመላክቷል። አለመግባባቱን ለመፍታት 26 ዙር ለመሸምገል ተቀምጠዋል። በማሸማገሉ ሂደት የተሳተፉት የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሁለቱን ማህበረሰቦች ለማቀራረብና በአካባቢው እረቀ-ሰላም ለማወርድ የከፈሉት መስዋዕትነት ቀላል አለመሆኑን በአጽኖኦት አስረድተዋል። የትኛውንም ውጣ ውረድና ጫና ተቋቁመው ሳይታክቱ ችግሩን የፈቱበት መንገድ ለዘመናዊው አስተዳደር ትምህርት የሚሰጥና በቅርስነት ለትውልድ የሚተላለፍ ሰናይ ተግባር መሆኑንም አስረድተዋል። ግጭቶች ቀደም ሲል የነበሩ፣ አሁንም ያሉና ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው። በተለያዩ ምክንያቶች የሚያጋጥሙ ግጭቶችን ፖለቲካዊ ትርጉም በመስጠት ከማጦዝ ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ተጠቅሞ ለማርገብ መስራት አዋጭና ተመራጭ መንገድ መሆኑን የጥናቱን ግኝት ዋቢ አድርገው ተመራማሪ ዮሐንስ መክረዋል። ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ለአገር በቀል እውቀቶች ተገቢውን ዕውቅና መስጠት ይገባል። አገር በቀል ዕውቀቶችን በትምህርት ሥርዓት ውስጥ አካቶ ለማጎልበት የተጀመረው አበረታች ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል። አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ አብሮነትን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው ያሉት ደግሞ የጂንካ ዩኒቨርስቲ የባህል ተመራማሪና የዩኒቨርስቲው የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ኤሊያስ ዓለሙ ናቸው። አክለውም ዘመናዊ ሕግን ተከትሎ በሚሰጡ ብያኔዎች አንዱ ወገን የሚደሰትበት ሌላኛው ደግሞ ቅር ተሰኝቶ የሚከፋበት ናቸው ይላሉ። በማህበራዊ ሸንጎ ግን ሁለቱም ወገን የሚደሰቱበት፣ ከልብ ይቅር ተባብለው ችግሮቻቸውን የሚፈቱበትና ዘላቂ እርቀ-ሰላም የሚያወርዱበት እንደሆነም ያስረዳሉ። ዶክተር ኤሊያስ አክለውም ይህም ማህበራዊ አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው የላቀ ነው። የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን ለመፍታትና በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በአገራችን ቱባ ባህሎች ውስጥ ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን መጠቀም ይገባል። በባህላዊ እሴቶቻችን ውስጥ ያሉ አገር በቀል ዕውቀቶች ቀጣይነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ እንዲውሉና ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆኑ ዕውቅና መስጠት፣ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ማካተት፣ በአግባቡ አደራጅቶና ሰንዶ ለትውልድ ማስቀመጥ እንደሚገባ አመላክተዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራን የሚጠበቅብንን ኃላፊነት በአግባቡ ልንወጣ ይገባል ይላሉ። አቶ መምህሩ ገዙሜ በጂንካ ዩኒቨርስቲ በሶሻል አንትሮፖሎጂ የትምህርት ክፍል የሶሽዮሎጂ መምህር ናቸው። አገር በቀል ዕውቀቶች ለአገራዊ ችግሮቻችን መፍቻ መንገዶች ናቸው ይላሉ። የሳይንሳዊ ምርምሮች ፅንሰ-ሀሳብ መነሻው አገር በቀል ዕውቀቶች እንደሆኑ ይጠቅሳሉ። በአገራችን በርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ቢኖሩም እንዳለመታደል በአግባቡ መጠቀም አልቻልንም ሲሉም ያክላሉ። እሳቸው እንዳሉት መንግሥት አሁን ለአገር በቀል ዕውቀቶች የሰጠው ዕውቅና ለአገር በቀል ዕውቀቶች መጎልበትና ጥቅም ላይ መዋል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ይህን ዕድል በመጠቀም አገር በቀል እውቀቶች ጎልተው እንዲወጡና በትምህርት ሥርዓቱ ተካተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት ይገባል። በተለይ የማህበረሰቡ የግጭት አፈታት ዘዴና በምክክር ችግሮችን የመፍታት ጥበብ የታሰበው አገራዊ የምክክር መድረክ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። በመሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ፣ ለኢትዮጵያውያን የአብሮነት ትስስርና መስተጋብር መጠንከር እንዲሁም ለአገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና እጅግ የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ተገንዝቦ ተገቢውን ዕውቅና በመስጠት መጠቀም ይገባል።
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ
Apr 2, 2023 1578
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ በሰለሞን ተሰራ በታሪክ ተመዝግበው የምናገኛቸው አያሌ መልካምና በጎ ነገሮች የመኖራቸውን ያህል በተቃራኒው ደግሞ የሰው ልጆች ግፍና በደል ሲፈጽሙና ሲያስተናግዱ ኖረዋል። በዚህም በተለይ በበደሉ ገፈት ቀማሾች ላይ የሚደርሰው ድንጋጤ፣ ሰቆቃና ሀዘን ሰዎችን ለበቀል እያነሳሳ ሌላ ጥፋት ሲያስከትል ማስተዋልም እንግዳ ነገር አይደለም። በዚያው ልክ ሰዎች የደረሰባቸውን ግፍና መከራ ለማራገፍ ፍትህን ሲሹና ሲጠይቁ ይስተዋላል። እምባቸው የሚታበሰው፣ ቁስላቸው የሚሽረው ለደረሰባቸው በደል ካሳ የሚሆን ፍትህ ሲያገኙ ብቻ እንደሆነም ያምናሉ። በርካታ አገራትም በታሪክ ውስጥ ላጋጠሟቸው ስብራቶች የሽግግር ፍትህን አማራጭ አድርገው በመጠቀም ለችግሮቻቸው መፍትሄ ያበጃሉ። እኤአ በ1970 ዎቹ መጀመሪያ በምስራቅ አውሮፓ እና ደቡብ አሜሪካ ተግባራዊ በተደረገው የሽግግር ፍትህ በጦርነትና በግፍ አገዛዝ የተበደሉ አካላት ፍትህ እንዲያገኙ የተደረገበት መንገድ ተጠቃሽ ነው። ከዚህ ጊዜ በኋላ የሽግግር ፍትህ በተለይ በመደበኛ የህግ ስርአት ብቻ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስቸግሩ ጉዳዮችን ጭምር በተጠያቂነት፣ በይቅርታ፣ በካሳ ወዘተ መፍትሄ በመስጠት የፍትህ ማስፈኛ መንገድ ተደርጎ ተወስዷል። የሽግግር ፍትህ ማለት በማህበረሰቡ ውስጥ በስፋት ለተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ምላሽ የሚሰጥበት አካሄድ መሆኑን ምሁራን ያስረዳሉ። ይህንን ሂደት ሰላማዊ፣ አካታችና ተደራሽ ለማድረግ የሁሉም ጥረትና አጋርነት ቀዳሚ መነሻ ሊሆን እንደሚገባውም ይገልጻሉ። የሽግግር ፍትህ በአንድ ጊዜ የሚያልቅ ሳይሆን ጊዜ የሚጠይቅና ዓመታትን ሊወስድ የሚችል ነው። ይህም ለተበዳዮች ፍትህ በመስጠት፣ ካሳ በመክፈል፣ የወደሙ ንብረቶችን መልሶ በመገንባትና በመሰል ሂደቶች ሊፈጸም ይችላል። የሽግግር ፍትህ ሀገራት ከብጥብጥ፣ ከፀብና ጥላቻ አዙሪት እንዲወጡ በማድረግ በኩል የማይተካ ሚና እንዳለው የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮዎች ያሳዩናል። በ2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ የፀደቀው የአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ማዕቀፍ፣ የሽግግር ፍትህ ሀገራት የተለያዩ መደበኛ እና ባህላዊ ወይም መደበኛ ያልሆኑ የፖሊሲ እርምጃዎችንና ተቋማዊ አሠራሮችን በመጠቀም የተፈጸሙ ጥሰቶችን፣ ክፍፍሎችንና አለመመጣጠኖችን ለማስወገድና ለደኅንነትም ሆነ ለዴሞክራሲያዊና ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሥርዓት ግንባታ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የሚደረግ ጠቃሚ እና አስፈላጊ ሂደት እንደሆነ ይገልጻል። የሽግግር ፍትህ በግጭት፣ በጦርነት ወይም ጨቋኝ ሥርዓት በነበረበት ወቅት ለተፈፀመ ጥቃት፣ መጠነ-ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና በደል የተሟላ መፍትሄ መስጠት መቻል ነው። ይህም በዋናነት ሙሉ ፍትህ የሚሰጥበትን መንገድ በመዘርጋት ዘላቂ ሰላም፣ እርቅ፣ መረጋጋት እና የህግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት መገንባት የሚቻልበትን ሁኔታ የሚመለከት ነው። በኢትዮጵያ ተግባራዊ ሊደረግ የታሰበውና በፖሊሲ አማራጭ ዝግጅት ሂደት ላይ የሚገኘው የሽግግር ፍትሕ በአራት ዋና ዋና ምክንያቶች አስፈላጊ መሆኑን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል። አንደኛው ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሀገራዊ አውድ ሲሆን በዚህም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ አለመረጋጋት፣ ግጭትና የእርስ በርስ ጦርነት ተከስቷል። ይህም ዜጎችን ለሞት፣ ለአካል ጉዳት፣ ለመፈናቀል ያጋለጠ መሆኑ በገፊ ምክንያትነት ይጠቀሳል። ለነዚህ ችግሮች ከዚህ በፊት የተሰጡ ምላሾች ሙሉ አለመሆናቸው የአጥፊዎችና የተጎጂዎችን ቁጥር ማብዛቱ፣ የበደሎች መደራረብ እና የጥፋቶች ማህበረሰባዊ ቅርጽ መያዝ በመደበኛው የፍትሕ ሥርዓት እና አካሄድ ፍትሕ መስጠትንም ሆነ ይቅርታ እና እርቅን ማከናወን አላስችል ማለቱ የሽግግር ፍትህ ትኩረት እንዲሰጠው አድርጓል። ሁለተኛው የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ማለትም ባለፉ በደሎች ይቅር ለመባባል፣ እርቅ ለማውረድ፣ ሕዝብ ለማቀራረብ፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እና ለተፈጸመ በደል እውቅና ለመስጠት አስፈላጊ በመሆኑ ነው። ሶስተኛው ምክንያት የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ሂደት ሳይተገበር የዴሞክራሲ ሽግግርም ሆነ ዘላቂ ሰላም ማስፈን አይቻልም የሚል ነው። የመጨረሻው በገፊ ምክንያትነት የሚጠቀሰው ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እና የሕግ የበላይነትን ለማስፈን የሽግግር ፍትህ ወሳኝ በመሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በነዚህ ምክንያቶች የሽግግር ፍትሕን ለማስፈን እየሰራች መሆኑ በበርካቶች ዘንድ በአዎንታዊ መልክ ይጠቀሳል። በተለይ የሽግግር ፍትህን ተግባራዊ ካደረጉ አገራት ተሞክሮ በመውሰድ ለውጤታማነቱ ከተሰራ በርግጥም አይነተኛ መፍትሄ ነው። ከአፍሪካ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ በቅርቡ ደግሞ ጋምቢያ የሽግግር ፍትህን ለችግሮቻቸው መፍቻነት ከተጠቀሙ አገራት መካከል ናቸው። ሩዋንዳ ሩዋንዳ እኤአ በ1994 በመቶ ቀናት ብቻ ከነበሯት 7 ሚሊዮን ዜጎቿ 800 ሺዎቹን በግፍ ተነጥቃለች። 2 ሚሊዮን የሚጠጉት በስደት ሀገራቸውን ለቀው ሲወጡ በዚህ የጭካኔ ተግባር ተሳትፎ ነበራቸው የተባሉ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ላይ ክስ በመመስረት ፍትህ ፊት አቅርባቸዋለች። በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት በሀገር ውስጥ ችሎትና በባህላዊ መንገድ በተዳኙት ወንጀለኞች ላይ የተሰጡት የፍትህ ውሳኔዎች አሁን ላይ ሀገሪቱን በዲሞክራሲና በሰላም እንዲሁም በብልፅግና መንገድ መራመድ እንድትችል አድርጓታል። ሩዋንዳውያን በቆየ ሀገራዊ ብሂላቸው ”ሁላችንም የአንድ አባትና እናት ልጆች ነን ይላሉ”። ይህንኑ ብሂል መመሪያቸው በማድረግ በሀገሪቱ ያሉት “ቱትሲ” እና “ሁቱ” የተባሉት ዋነኛ ብሄሮች በአብሮነት ለዘመናት ኖረዋል። ሩዋንዳ በጀርመን የቅኝ አገዛዝ ስር እንደወደቀች የዘር ልዩነቱን ወደፊት ያመጡት ቅኝ ገዥዎች ሁለቱን ብሄሮች የሚያጋጩ ሴራዎችን በመጎንጎን ቱትሲዎችን መግደል የፖለቲካቸው ስልት ማስፈጸሚያ አደረጉት። ይህ ከፋፋይ የፖለቲካ ሴራ በቤልጂየም የእጅ አዙር አገዛዝ ዘመንም እንደቀጠለ ይነገራል። በዚህም ማንነትን መሰረት ያደረገ የፖለቲካ አደረጃጃት፣ የመታወቂያ ወረቀት፣ ቱቲስዎችን በስልጣን ወደፊት ማምጣትና ሁቱዎችን አሳንሶ መመልከትን ባህል አደረጉት። በዚሁ መርዘኛ ሀሳብ መነሻነት ከነጻነት በኋላ እኤአ ከ1959 እስከ 1967 አካባቢ በመንግስት በተደገፈ የዘር ማጥፋት 20ሺ የሚጠጉ ቱትሲዎች ሲገደሉ 300ሺ የሚጠጉ ሀገራቸውን ለቀው ተሰደዱ። በዚህም እኤአ በ1987 በቱትሲዎችና ለዘብተኛ ሁቱዎች የተቋቋመው የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር እኤአ በ1993 የመንግስትን ስልጣን ለመጋራት በቃ። ነገር ግን እኤአ በሚያዚያ 6 ቀን 1994 የሀገሪቱ መሪ የነበሩት ሃባይሪማና በቅጥረኞች በመገደላቸው በሀገሪቱ አመጽ እንዲቀጣጠል ምክንያት ሆነ። ይህን ተከትሎ “ኢንተርሀሞይ” በመባል የሚጠራው የሚሊሽያ ቡድን በቱትሲዎችና በለዘብተኛ ሁቱዎች ላይ ዘመን የማይሽረው ግፍና ጭካኔ በመፈጸም 800ሺ የሚጠጉትን ከምድር ላይ ለዘለአለሙ አሰናብቷቸዋል። ይህ ደግሞ የዘር ማጥፋት ወንጀል በመሆኑ አጥፊዎቹ በተለያዩ የፍትህ አደባባዮች ተከሰው ቅጣታቸውን ለመቀበል በቅተዋል። ነገር ግን ይህ ብቻውን በህዝቡ ውስጥ ስር የሰደደውን ቁስል እንዳማይሽረው በመታመኑ ሩዋንዳ የሽግግር ፍትህን በመከተል አመርቂ ስራ ሰርታለች። በተለይም ክስና ይቅርታ ትልቅ ቦታ ነበራቸው። በክስ ሂደቱ ሁሉንም ተጠያቂ ማድረግ ቢከብድም በዋናነት ተሳታፊ የነበሩትን በመለየትና ተጠያቂ በማድረግ ፍትህ እንዲሰፍን ተደርጓል። መንግስት ውጫዊና ውስጣዊ ግፊት ቢበዛበትም ከፍተኛ ግፍ የፈጸሙትን በመለየት እንዲቀጡ አድርጓል። ይቅርታውንም በተጠና መንገድ በማከናወን ለጥቂቶች ምህረት አድርጓል። በጊዜ ሂደት የእስራት ጊዜአቸውን ላገባደዱ፣ ለአዛውንቶች፣ ለታማሚዎችና ለወጣቶች ምህረት በማድረግ ቁርሾው እንዲሽር ተደርጓል። ምህረት የተደረገላቸው ሰዎች ስለብሄራዊ እርቅ፣ አብሮነት፣ ሀገራዊ ማንነትና ሰብዓዊ ክብር እንዲማሩ በማድረግ እርቁን ሙሉ ማድረግ ተችሏል። የሩዋንዳ የሽግግር ፍትህ በዋናነት እውነትን ማፈላለግ፣ ነገሮችን መልሶ ማስታወስ ወይም የመታሰቢያ ቦታዎችን በመመስረትና ቀን በመሰየም ሁኔታው ታስቦ እንዲውል ማድረግ፣ መልሶ ማቋቋምና እርቅ ማውረድ የተቋማት ማሻሻያ ማድረግ ላይ ያተኮረ ነበር። ሴራሊዮን እኤአ ከ1991 አስከ 2002 የዘለቀው የሴራሊዮን የእርስ በርስ ግጭት በትንሹ የ100ሺ ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ አልፏል። ሌሎች በ100ሺ የሚቆጠሩ ዜጎችን ለከፋ የአካል ጉዳት፣ ድህነትና የአዕምሮ መቃወስ ዳርጓል። ግጭቱ የተጀመረው ራሱን “የተባበሩት አብዮታዊ ቡድን” ብሎ በሚጠራው የታጣቂዎች ስብስብ ሲሆን በወቅቱ ቡድኑ በላይቤሪያ መንግስት ይደገፍ እንደነበር ይነገራል። የተቃውሞአቸው መነሻ ደግሞ የመንግስት ብልሹ አስተዳደር፣ የገጠሩ ማህበረሰብ ከኢኮኖሚና ፖለቲካ ተሳትፎ መገለል እና መጠነ ሰፊ የህግ ጥሰቶች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ። የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሃብት በተለይም የአልማዝ ማዕድኗን በህገወጥ መልኩ ሲበዘብዙ የነበሩ አመራሮች ቁርሾውን በማባባስ ህልውናቸውን ለማስቀጠል ቢጥሩም እኤአ በ2002 በተደረሰ የሰላም ስምምነት ከ 76 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን በማስረከብ ህብረተሰቡን እንዲቀላቀሉ ተደርገዋል። በዚያው ዓመት የሴራሊዮን የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን የተቋቋመ ሲሆን በተመሳሳይ የሴራሊዮን ልዩ ችሎት ተመስርቷል። ሴራሊዮን በእርስ በርስ ግጭት ውስጥ በነበረችባቸው 12 ዓመታት አራት መፈንቅለ መንግስት የተካሄደባት ሲሆን የስልጣን መንበሩን የተፈራረቁበት የተለያዩ ወታደራዊ አመራሮች ለችግሩ መፍትሄ ከማበጀት ይልቅ በቤንዚን ላይ እሳት የሚያርከፈክፉ ሆነው ታይተዋል። በሴራሊዮን ለደረሰው እልቂት እኩል ኃላፊነት የሚወስዱት መንግስትና ታጣቂዎች በወቅቱ ሴቶችን በመድፈር፣ ህፃናትን በግዳጅ ለጦርነት በመመልመል፣ ንብረት በማውደምና በ100ሺ ለሚቆጠሩ ሰዎች መሞት ተጠያቂ ተደርገዋል። ከዚህ ባለፈ በቅድሚያ ታጣቂዎችን የጦር መሳሪያ ለማስፈታት የተሄደበት ርቀት ለሰላም መስፈን ትልቅ እገዛ ማድረጉ የሚገለጽ ሲሆን ከ70 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎችን መሳሪያ ማስፈታት መቻሉ ግጭቱን ለማስቆም በራሱ ታላቅ ስኬት ነበረው። በወቅቱ ግፉን የፈጸሙት ታጣቂዎች በመንግስት ቅጣታቸውን እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን ህብረተሰቡም ወንጀለኞችን ከማህበረሰቡ በማግለል የስነ ልቦና ቅጣት እንደጣለባቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በዚህም ታጣቂዎቹን ወደ ህብረተሰቡ መልሶ ለመቀላቀል የተደረገው ጥረት በፈተና ቢታጀብም በህዝቡ ይሁንታ ውጤታማ ሆኗል። በሴራሊዮን የሽግግር ፍትህን ለማስፈን የተቋቋሙት የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን፣ የሴራሊዮን ልዩ ፍርድ ቤት፣ በፀጥታ ተቋማት ላይ የተደረገው ማሻሻያ፣ የመልሶ ማቋቋምና የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ምስረታ ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው። የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን በተሰጠው ስልጣን መሰረት ተጎጂዎችን ከሰቆቃ መታደግና ችግሩን በዕርቅ መፍታት፣ ብዙሀኑ ላይ ለደረሰው ግፍ ምላሽ መስጠት፣ ግፉ በቀጣይ እንዳይደገም መፍትሄ ማበጀት ላይ አተኩሮ ሰርቷል፡፡ በዚህም ከተጎጂዎች ቃለ ምልልስ በመነሳት በደረሰበት ድምዳሜ የመንግስት አካላት የመልካም አስተዳደር መጓደል፣ ሙስና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ከነፃነት በኋላ የነበረው አመራር ብቃት ማነስ ለብጥብጡ መንስኤ እንደሆነ አመላክቷል። ልዩ ፍርድ ቤቱም በቅድሚያ ተጎጂዎችን ሰብስቦ በማናገር እንዲሁም የሲቪል ማህበራትን ህብረተሰቡንና መገናኛ ብዙሃንን በማካተት ሁሉንም የሚያስማማ ውሳኔ በመስጠት ችግሩ ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ መፍትሄ እንዲያገኝ አስችሏል። የመልሶ ማቋቋም ሂደቱ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበርና ልዩ በጀት በመመደብ የተከናወነ ሲሆን የተጎጂዎችን ሰቆቃ ሊጠግን በሚችል መልኩ መተግበሩንም ብዙዎች ይመሰክራሉ። በዚህም ተጎጂዎች ነፃ የጤና አገልገሎት፣ ትምህርት፣ መኖሪያ ቤትና መቋቋሚያ እንዲያገኙ ተደርጓል። በአብነት የተነሱት የሩዋንዳና ሴራሊዮን ተሞክሮዎች የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭቶችን ያስተናገዱ ሀገራት የተሻለ ነገን እንዲገነቡ ሁነኛ መፍትሔ ስለመሆኑ አመላካች ናቸው። በተመሳሳይ የሽግግር ሂደት ያለፉና ተሞክሮ ያላቸው የደቡብ አፍሪካ እና ጋምቢያ ምሁራንም ይህንኑ እውነት የሚያረጋግጥ ሀሳባቸውን ለኢዜአ ሰጥተዋል። በደቡብ አፍሪካው ፍሪታውን ዩኒቨርሲቲ የፍትሕና ዕርቅ ኢንስቲትዩት ኃላፊ እና በአፍሪካ ጥናትና ምርምር የካበተ ልምድ ያላቸው ፕሮፌሰር ቲም ሙሪቲ በአፍሪካ ሽግግር ፍትህ ዙሪያ ጥልቅ ምርምር አድርገዋል። ኢትዮጵያ ታሪካዊና የአፍሪካ ተምሳሌት ሀገር ናት የሚሉት ፕሮፌሰሩ፤ የገጠማትን ችግር ለመፍታት የሽግግር ፍትህ ሂደት መጀመሯን አድንቀዋል። የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭትና ግፎችን ባሳለፉ ማህበረሰቦች ትናንትን በይቅርታ የነገውን ተሰፋ ለመሻገር አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን በማንሳት ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ፣ ባርነት እና ቅኝ ግዛት የጭቆና ስርዓት ነጻ ስትወጣ ስርዓቱ በጥቁሮች ላይ ለፈጸመው ግፍ፣ መገለልና ብዝበዛ መፍትሄ ለመስጠት ሽግግር ፍትህ ሂደት መተግበሩን ይጠቅሳሉ። ፕሮፌሰር ሙሪቲ፤ የወቅቱ ፕሬዝዳንት ኔልሰን ማንዴላ በጥቁሮች ላይ የተፈጸሙ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት መልክ ለመስጠት ብሎም ህዝባዊ አብሮነት እንዲቀጥል በሊቀጳጳስ ዴዝሞንድ ቱቱ መሪነት የዕውነትና ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን መቋቋሙን ያስታውሳሉ። የሽግግር ፍትሕ ሂደቱ ከአፈጻጸም ጋር የተያያዙ ክፍተቶች ቢኖሩበትም አካታችና የአገሪቱን የቀጣይ ጉዞ ለመቀየስ መሰረት የጣለ እንደነበር ገልጸዋል። ይህም ኢትዮጵያ ተሞክሮ ልታደርገው የምትችለው ነው ይላሉ። በጋምቢያ በቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ያህያ ጃሜህ ዘመነ መንግስት ለ22 ዓመታት የተፈጸሙ ግፎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት የፈቱት የዕውነት፣ ዕርቅና ካሳ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ጋምቢያዊው ዶክተር ባባ ጋሌህ ጃሎው፤ የሽግግር ፍትህ አስፈላጊነት በተለይም ኢትዮጵያን ለመሰሉ ሀገራት አጠያያቂ አለመሆኑን ይላሉ። በተመሳሳይ በጋምቢያ አምባገነን መንግስት የተፈጸሙ በደሎችን መልክ ለማስያዝ የተቋቋመው የዕውነት፣ ዕርቀ ሰላምና ካሳ ኮሚሽን ዜጎች ዕውነቱን እንዲረዱ፣ በዳዮች እንዲጠየቁና ተበዳዮች እንዲካሱ የሚያስችል ሰነድ ለሀገሪቷ መንግስት ማቅረቡን ዶክተር ባባ ጋሌህ ይገልጻሉ። እነዚህ ምሁራን ኢትዮጵያ ለማድረግ ያሰበችው የሽግግር ፍትህ ሂደት ከአፍሪካ ሕብረት የሽግግር ፍትሕ ፖለሲ እና የሀገራትን ልምድ የቀመረ፣ አካታች፣ ተበዳዮችን የሚክስና ሀገርና ህዝብ ወደፊት በሚያሻግር አግባብ እንዲፈጸም አስተያየታቸውን ጠቁመዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራኑ ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ለሚመለከተው አካል እንደሚያጋሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያን ባለፉት ጥቂት ዓመታት በህዝቦች የተባበረ ክንድ ለውጥ በማምጣት አዲስ ምእራፍ የጀመርንበት፣ አዲስ መንግስት ስልጣን ተቀብሎ ያለፉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በይፋ በማመን ይህንኑ ለማሻሻል ቃል የገባበት፣ የዲሞክራሲ ሽግግር ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት የተጀመሩበት እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት የደረሱ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ለማለፍ መንገድ የጀመርንበት ወቅት ላይ መሆናችን ይታወቃል። የሽግግር ፍትህ የተበዳዮችን እምባ ከማበስ ባለፈ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ በማስቀመጥ ከቂም በቀል የጸዳ ትውልድ ለመፍጠርና ለአገረ መንግስት ግንባታ በጋራ ለመሰለፍ መፍትሄ መሆኑን ከላይ የተጠቀሱት አብነቶች ምስክሮች ናቸው። ለአፍሪካ ጉዳዮች አፍሪካዊ መፍትሄን የምታስቀድመው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገራት ተሞክሮዎችን በመቀመር፣ ካለፈችባቸው መንገዶች ትምህርት በመውሰድ፣ ውጤታማ የሆነ የሽግግር ፍትህ ስርዓትን እውን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል። የሽግግር ፍትሕ በተለይም በሽግግር ላይ ያሉ ሀገራት ህዝቦች ከነበሩበት ግጭት እንዲሁም ከደረሰባቸው ግፍ እና ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ወጥተው ወደ አዲስ ሰላማዊ እና አብሮነት ጉዞ ለመጀመር የሚደረግ የፍትሕ ክዋኔ አይነት በመሆኑ በትኩረት ሊሰራበት ይገባል።          
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 2764
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
ትንታኔዎች
የረቂቅ ሙዚቀኛዋ መናኒት ሲታወሱ
Jun 2, 2023 114
የረቂቅ ሙዚቀኛዋ መናኒት ሲታወሱ አየለ ያረጋል መንደርደሪያ... እማሆይ ጽጌማርያም 'ዓለም በቃኝ' ብለው በምንኩስና ሕይወት መንነዋል። በቅድመ ምነናም ሆነ ድሕረ ምነና ሕይወታቸው ግን በረቂቅ ሙዚቃ ከመራቀቅ ቦዝነው አያውቁም ነበር። ለዚህ ነው 'የረቂቅ ሙዚቃ ተራቃቂዋ መናኒት' የሚሰኙት። በእማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ ፋውንዴሽን ድጋፍ ሰሞኑን በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 'ዝክረ እማሆይ ጽጌማርያም' መርሐ ግብር ተደርጎ ነበር። የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች መርሐ ግብሩን አሰናድተዋል። በሕይወት ዘመናቸው ከ300 በላይ የረቂቅ ሙዚቃ ስራዎችን ለአድማጭ ጆሮ ያበረከቱት እማሆይ ጽጌማርያም ያረፉት ባሳለፍነው መጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ነበር። ስርዓት ቀብራችው የተፈጸመውም ለ40 ዓመታት በገዳማዊ ሕይወት በኖሩባት ሀገረ-እስራኤል ኢየሩሳሌም ነው።   የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሙዚቃ ትምህርት ክፍል ስያሜውን 'እማሆይ ጽጌማርያም የሙዚቃ ትምህርት ክፍል' በሚል ሰይሟል። እኛም እማሆይን በወፍ በረር መዘከር ወደድን!! የ'የውብዳር' ሙዚቃ ልክፍት ሙዚቃ ኅይል ነው-ውስጥን የሚፈነቅል፤ መንፈስን የሚሰረስር። የየውብዳር የሙዚቃ ውበትና ቃና ልክፍትም በዘመነ ደቂቅነት የተጸነሰ ነው። የሙዚቃ ፍቅራቸው ጠሊቅ፣ ስራቸውም ረቂቅ ነው። ግና በጨቅላነት የ'ግዳይ ጣይ' አዳኞችን ባህላዊ ዜማ ተከትለው ሮጠዋል። በቤተ ክርስቲያን ማህሌታዊ ዜማዎች ቀልብና ልባቸው ተማርኳል። የልጅነት ዕዝነ ልቦናቸው በሙዚቃ ቃና ተለክፏል። የደቂቅነት ዐይነ ልቦናቸው ተፈጥሯዊ ውበት በረቂቅ ሙዚቃ እንዲራቀቁ ሰበብ ሆኗቸዋል። 'ከሰፈር እስከ ማዶ-ሀገር' ኑረታቸው በዕዝነ ልቦናቸው ያቃጨለ የድምጽ ርግብግቢት በረቂቅ ሙዚቃ እንዲመንኑ መሰረት ሆኗቸዋል። የየውብዳር ዑደት ሕይወት ከዓለማዊ ወደ ሰማያዊ ሕይወት ብቻ ሳይሆን በመሳሪያ ወደ ተቀነባበሩ ረቂቅ ሙዚቃ ዳርቻም መንኗል። የወላጅ እናታቸው ካሳዬ የለምቱ በገና ደርዳሪነት፣ የአባታቸው ከንቲባ ገብሩ ደስታ የረቂቅ ሙዚቃ አጣጣሚነት በሙዚቃ ጣዕም የመለከፋቸውን ልክ አንሮታል። ሙዚቃን "የስሜት መግለጫ ቋንቋዬ፤ የሀዘንና ደስታዬ ጓድ” ይሉታል-የኋላዋ እማሆይ ጽጌማርያም፤ የያኔዋ የውብዳር ገብሩ!   እማሆይ ጽጌማርያም ውልደታቸው ከደህና ቤተሰብ መደብ ነው። አባታቸው ከንቲባ ገብሩ ደስታ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ጉልህ አሻራ አላቸው። ዕውቁ የታሪክ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ከንቲባ ገብሩ ደስታን ከ20ኛው ከፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ትምህርት ፋናወጊዎች መካከል አንዱ ናቸው ይሏቸዋል። በአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግስት በጣና ሐይቅ ምዕራባዊ ዳርቻ አለፋ ጣቁሳ የተወለዱት ገብሩ ደስታ ገና በልጅነታቸው በሚሲዮናዊያን ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ተወስደው የተማሩ፤ በተለያዩ ሀገራት ተዘዋውረው ያስተማሩና በኋላም ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው ከአጼ ዮሐንስ እስከ አጼ ኅይለስላሴ ዘመነ መንግስት ሀገራችውን ያገለገሉ ጎምቱ ባለታሪክ ናቸው። ከንቲባ ገብሩ ደስታ የሀረር እና የጎንደር ከንቲባ፤ በአሜሪካና በአውሮፓ ሀገራት የዲፕሎማቲክ ልዑክ መሪ፣ የመጀመሪያው ሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ በኋላም ዋና አፈ ጉባዔ ነበሩ። ከንቲባ ደስታ በየዘርፋቸው ኢትዮጵያን ያገለገሉ ልጆችን በእግራቸው ተክተዋል። ኮሎኔል ዳዊት ገብሩ፣ ገነት ገብሩ፣ ደስታ ገብሩ፣ የውብዳር ገብሩና ስንዱ ገብሩ ተጠቃሽ ናቸው። የውብዳርም የሕይወት ውጣውረድና አቀበት አልፈው፤ መክሊታቸውን ፈልገው የኖሩ ተምሳሌታዊ መናኒት ሆነዋል።   ልደታቸው ታኅሣሥ 13 ቀን 1916 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ነበር። ገና በ6 ዓመታቸው በኋላ የጦር አርበኛ፣ ፀሐፊ ተውኔት፣ ደራሲ፣ የመጀመሪያዋ ሴት የፓርላማ ተመራጭና ዲፕሎማት ከነበሩት ታላቅ እህታቸው ስንዱ ገብሩ ጋር ስዊዘርላድ ለትምህርት አቀኑ። የውብዳር ወደ የባሕር ማዶ ጉዟቸውን ሲያስታውሱ "ከጅቡቲ ጉዞ በጀመርንበት ጀልባ ላይ የተሳፈርን ብቸኛዎቹ ጥቁሮች እኛ ነበርን። በዚያ ድቅድቅ ጨለማ ሰማዩ ላይ የፈካችውን ሙሉ ጨረቃና ማዕበል የሚንጠውን ባህር በተመስጦ ነበር የምመለከተው። ከዚያ በመነሳት በኋላ ላይ “የባህር ላይ ዘፈን- Song of the sea' የሚለውን ሙዚቃ ደረስኩ" ብለው ነበር። የተፈጥሮን ውበት ልክ በሙዚቃ ኅይል በመግለጥ የተካኑ ጠቢብ ናቸውና ገጠመኛቸውን በረቂቅ ሙዚቃ ተራቀቁበት። በስዊዘርላንድ 'ሞንትሚሬል ትምህርት ቤት' በዕድሜ ትንሿ ተማሪ ነበሩ። አንድ ዕለት የቫዮሊን ድምፅ ሰምተው ተማረኩና መጫወት ጓጉ። በሌላ ዕለት አንዲት ፒያኖ አግኝተው ቁልፉን በጣቶቻቸው እየደቆሱ ምስቅልቅል ስሜታቸውን አስተጋቡበት። ሙዚቃውንም 'ማዕበል' ብለውታል። እናም ከቀለም ትምህርቱ በተጓዳኝ ቫዮሊንና ፒያኖ አጠኑ።ገና በ10ኛ ዓመታቸው የመጀመሪያ የሙዚቃ ትርዒት አቀረቡ። “ከንቲባ ገብሩ የኢትዮጵያ ባለውለታ” በተሰኘው የወንድማቸው ኮሎኔል ዳዊት ገብሩ መጽሃፍ ውስጥ የተጠቀሰው የእማሆይ ጽጌማርያም ማስታወሻ "... በሰባት እና በስምንት ዓመት ዕድሜዬ፣… ከሥነ ፍጥረት ጋር ወዳጅነት ነበረኝ፡፡ አበቦች ውብ ልዕልቶች፣ ዛፎች… እንደ ዘበኞቻቸው፣ ነፋስ… ወጣት መልዕክተኛ፣ ፀሐይ… ደግሞ የዓለም ኹሉ ንግሥት ኾነው ይታዩኝ ነበር፡፡ ያን ጊዜ በአዳሪ ትምህርት ቤቱ ውስጥ በኔ ዕድሜ ልጅ ስላልነበረ…ብቸኝነት የሕጻንነት ጓደኛዬ ኾኖ አብሮኝ አደገ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አንድ የኀዘን ስሜት፣ የመንፈስ ዕረፍት ዕጦት አደረብኝ፡፡ ሙዚቃ እወድ ነበርና ስሰማው የኀዘን ስሜት ያመጣብኝ ነበር" ይላል።   የፒያኖ ትምህርታቸውን አዲስ አበባ ተመልሰው በእቴጌ መነን አዳሪ ትምህርት ቤት አጠናክረዋል። ልምምዳቸው ግን በጣሊያን ወረራ ምክንያት ተቋረጠ። የ13 ዓመት ልጃገረድ ነበሩ። በፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ከነቤተሰቦቻቸው በፖለቲካ እስረኛነት ወደ ኢጣሊያ አሲናራ ደሴት ወህኒ ቤት ተጋዙ። በግዞት ሆነው ግን ከካቶሊክ ሲስተሮች ጋር ኦርጋን ይጫወቱ ነበር። ሙዚቃ ልክፍታቸው ነውና!! ከሶስት ዓመት ግዞት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ቢመለሱም የሙዚቃ ቃና ልክፍታቸው ግን ወደ ውጭ ሀገር ተመልሶ የመማር ጉጉታቸው ናረ። እናም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጸሃፊነት ስራቸውን አቋርጠው የትምህርት ዕድል ተፈቅዶላቸው ወደ ግብጽ ካይሮ አመሩ። በካይሮ ቆይታቸው “ቬሉኑስ ኮንሰርቫቶሪ ኦፍ ሉቺኒያ” በተሰኘ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ቫዮሊንና ፒያኖ ተምረው ዲፕሎማ ተቀበሉ። "በየዕለቱ ቫዮሊን ለአራት ሰዓታት፤ ፒያኖ ደግሞ ለአምስት ሰዓታት ያህል እጫወታለሁ። በየመሃሉ ደግሞ ወደ ሬስቶራቶችና ፊልም ቤቶች እየሄድኩ እዝናና ነበር" ብለዋል በአንድ ወቅት ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ። በካይሮ ሙቀት ምክንያት ወደ አዲስ አበባ እስኪመለሱ ድረስ የሙዚቃ ናፍቆታቸውን በቅጡ አጣጠመዋል። የውብዳር የሙዚቃ ጥማቸውን አልቆረጡም። አውሮፓ ተሻግሮ የመማር ፍላጎታቸው አልተቋረጠም። በእንግሊዝ ነፃ የሁለት ዓመት የትምህርት ዕድል ቢያገኙም ሳይፈቀድላቸው ቀረ። ክፉኛ አዘኑ። ከከባድ ህመምና ድባቴም በህክምና ዳኑ። በሂደትም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውብ ዝማሬዎች እየተሳቡ መጡ። የሙዚቃ ትምህርት ምናኔያቸው ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ምናኔ ተለወጠ። ውሎ አዳራቸው ቤተ መቅደስ ሆነ። ".... የዚህ ዓለም ፍቅር እና የመኖር ፍላጎት ከኅሊናዬ ፈጽሞ ተወገደ" ብለዋል በማስታወሻቸው። ከ'የውብዳር ወደ 'እማሆይነት' ምናኔ በወቅቱ የ19 ዓመት ልጅ ነበሩ። በአንድ ዕለት ወጣቷ የውብዳር ለንግስ በዓል ከአዲስ አበባ ወሎ ግሸን ማርያም ተጓዙ። ለሁለት ዓመታት ሰዓታትና ቅዳሴ ሳያቋርጡ ተማሩ፤ ፀለዩ። ታሪክን እንዲህ ያወሳሉ። “…ሁሉንም ነገር ዕርግፍ አድርጌ ትቼ ከዓለም ተነጠልኩ። እቅዴ በጫካ ውስጥ ባህታዊ ሆኜ ኑሮን ለመግፋት ነበር። ግሸን ማርያም እንደደረስን መነኮሳቱን ቀሳውስቱንና አቡነ ሚካኤልን አገኘሁ። ለመመንኮስ እንደመጣሁ ለአቡነ ሚካኤል ነገርኳቸው። እርሳቸው ግን ፈቃደኛ አልነበሩም። እኔም ውሳኔዬ መሆኑን አስረግጬ ነገርኳቸው.... በሀሳቤ የፀናው መሆኑን ካረጋገጡ በኋላ ተስማሙ" ይላሉ።   እናም መስከረም 21 ቀን 1940 ዓ.ም. በ20ዎቹ ዕድሜያቸው መጀመሪያ ለማዕረገ ምንኩስና በቁ። 'የውብዳር' የተሰኘው ስማቸው በክርስትና ስማችው እማሆይ ጽጌማርያም ተቀየረ። እማሆይ ሙሉ ጊዜያቸውን ለሙዚቃ ቅማሬ እና መንፈሳዊው ግልጋሎት ሰጡ። "... ሙዚቃውን እንዳላጣው ፈለገ። ሁሉም በእርሱ ሞገስ ነው የሆነው" ይላሉ። ለአስር ዓመታት በግሸን ማርያም ገዳም ያለ ጫማ ተጉዘዋል። እማሆይ ፅጌማርያም በመንፈሳዊ ሕይወትም፤ በረቂቅ ሙዚቃም መንነዋል። የሙዚቃ ስራዎቻችውም ከአፍሪቃ ቀንድ አልፎ በምዕራቡ ዓለም ናኝቷል። ስራዎቻቸውም ታዲያ ከመንፈሳዊ ተመስጦ ባሻገር ለሰብዓዊ ርዳታ ተልዕኮ የሚውል ነበር። እማሆይ ጽጌማርያም ከመጀመሪያ አልበማቸው ጀምሮ ከአልበም ሽያጭ የተገኘ ገቢ ለግላቸው ተጠቅመው እንደማያውቁ ይነገራል፤ ለህጻናት እርዳታ ያውላሉ እንጂ። “በደርግ ዘመን ከታተመው አራተኛ አልበሜ ያገኘሁትን ገንዘብም ኢየሩሳሌም ውስጥ ያለችውን የኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ለመደገፍ አዋልኩት። ዘቪዥነር ከተሰኘው አልበሜ ያገኘሁትን ገንዘብም በወቅቱ የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ከወዲያ ወዲህ ይል ለነበረው ኢጂኤም ፋውንዴሽን ድጋፍ አድርጌበታለሁ። ሶቨኔርስ የተሰኘ ስድስተኛ አልበሜ የተገኘው ገቢም በኢየሩሳሌም ለሚገኝ ቤተክርስቲያን ድጋፍ የሚውል ነው” ብለዋል እማሆይ።   ሙዚቃ በሸክላ ለማስቀረጽ የወሰኑትም በጎንደር በነበሩበት ወቅት ከቅዳሴ መልስ ባጋጠማችው ክስተት እንደነበር እንደህ አውስተዋል። "ጎንደር በነበርኩበት ጊዜ በየቤተክርስቲያኑ የማይጠገበውን ማኅሌት ሰምቼ ስመለስ፤ እደጅ የአገር ቤት ተማሪዎች በየሜዳው ጥቅልል ብለው ተኝተው አያለሁ፡፡ ብጠይቅ ሌሊት ቤተክስቲያን ያደሩ ናቸው፣ ቤት የሌላቸው፡፡ በዚህም ልቤ ተነካ፣ አዘንኩ፡፡ እኔ ሀብት የለኝ፤ ያለችኝ ያቺው ሙዚቃዬ፡፡ ስለዚህ እስኪ ሙዚቃዬን ላስቀርጽ እና ሽያጩን እነዚህ ልጆች ገብተው በነጻ የሚያድሩበት ቤት ላቋቁም አልኩ" ይላሉ። እማሆይ ጽጌማርያም እስከ ሕልፈተ ሕይወታቸው ድረስ ለአራት አስርት ዓመታት ገዳማ ኑሯቸውን በሀገረ-እስራኤል ኢየሩሳሌም በሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት አድርገው ቆይተዋል። 'የፒያኖዋ እመቤት' ረቂቅ አሻራዎች እማሆይ ጽጌማርያም የአንድ ምዕተ ዓመት ምድራዊ ሕይወት ዘላለማዊ አይረሴ ስራዎች አቅርበዋል። በፒያኖ ረቂቅ ሙዚቃ ቅማሬያቸውም 'የፒያኖዋ እመቤት' የሚል ስም አትርፈዋል። እማሆይ ጽጌማርያም ከዓለማዊ ወደ መንፈሳዊ ሕይወትን የዘነቁ፣ ሀገርኛ ወደ ባህር ማዶ ረቂቅ ጥበብን አዋህደው የተራቀቁ፣ የፒያኖ ቀማሪ፣ የቫይሊን ደርዳሪ፣ የኖታቸው ቃና መንፈስን ኮርኳሪ፣ ስክነትና ጥልቅ ተመስጦን መካሪ፣ መክሊታቸውን የኖሩ፣ በስራዎቻቸው አድማስ ዘለል አድናቆትና ሞገስ የተቸሩ፣ ... የረቂቅ ሙዚቃ እመቤት ናቸው። የኢትዮጵያን ሙዚቃ ለመጀመሪያ ጊዜ በጀርመን ሀገር በሸክላ ካስቀረጹት ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ቀጥሎ እማሆይ ፅጌ ማርያምም የኢትዮጵያን ክላሲካል ሙዚቃዎች በሲዲ በማስቀረፅ ለዓለም ሕብረተሰብ ያስተዋወቁ የመጀመሪያዋ እንስት ናቸው። በአጠቃላይ ስድስት የሙዚቃ አልበሞችን አሳትመዋል። በ1955 ዓ.ም. “ሆምለስ ወንደረር-ቤት አልባ መንገደኛ” እና “ሶንግ ኦፍ ዘ ሲ-የባሕሩ ዜማ” ሁለት አልበሞች ጀርመን ውስጥ አስቀርጸዋል። ዕውቁ የሙዚቃ ሊቅ ሞዛርት በተጫወተበት ፒያኖ የመጫወት ዕድል ገጥሟቸዋል። የቤቶቨንን፣ የሞዛርትንና ሽትራውዝን ጨምሮ የአያሌ ክላሲካል ሙዚቃ ሊቆችን ስራዎች ተጫውተዋል።   ከ1950ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን አቅርበዋል። በኢየሩሳሌም ሁለት ኮንሰርቶች አቅርበዋል። ስራዎቻቸው 'ኢትዮፒክስ' በተሰኘው የፈረንሳዊው አቀናባሪ ፍራንሲስ ፋልሴቶ ተከታታይ የሙዚቃ አልበሞች ውስጥ ተካተዋል። የእማሆይ ጽጌማርያም ሙዚቃ 'ፓሲንግ' የተሰኘው የሆሊውድ ፊልም እና የፔጆ መኪና ማስታወቂያን አጅቧል። እማሆይ ስራዎቻቸውና ስብዕናቸውም የተጣጣመ ነው። በ1950 ኮንሰርታቸው በወሎ ረሀብ አደጋ ተጎጂ ዜጎች ድጋፍ ለማሰባሰብ ታልሞ በተዘጋጀው ኮንሰርት ላይ የቬትሆንን 'ፓቲክ' እና 'ሆምለስ ወንደረር' የተሰኘ ስራዎች ተጫውተዋል። ወደ ወሎ ሂደው በርሀብ አለንጋ የተገረፉ ህጻናትን በአካል በማየት ‘የድርቅ እልቂት-famine disaster' የተሰኘ ሙዚቃ ደርሰዋል። የፒያኖዋን እመቤት ሥራዎች ለቀጣይ ትውልድ ለመዘከር የተቋቋመው 'የእማሆይ ጽጌማርያም ፋውንዴሽን' በረቂቅ የሙዚቃ ዘርፍ ዕድገት የበኩሉን ሚና ሲጫወት ቆይቷል። በእማሆይ የሙዚቃ መንበር ለመቀመጥና ለረቂቅ ሙዚቃ መራቀቅ የሚሹ ወጣቶችን ይደግፋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት እና በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር በሚገኘው የሙዚቃ ትምህርት ክፍል ፒያኖን ጨምሮ ለሙዚቃው እምርታ የሚያግዝ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል። ለዓመታት ሲገለገሉበት የነበረው ፒያኖም ለያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት እንዲሰጥ በመናዘዛቸው በቅርቡ ለትምህር ቤቱ ተሰጥቷል። ከሕልፈተ ሕይወታቸው በኋላ “ኢየሩሳሌም” የተሰኘ 10 የፒያኖ ትራኮች የያዘ አልበማቸው በሚሲሲፒ ሪከርድስ አማካኝነት እንደሚወጣ ተገልጿል። እማሆይን የሚዘክሩ መፃሕፍት በተለያዩ ወገኖች ታተመዋል፤ ጥናትና ምርምር ስራዎችም እየተሰሩ ነው። እማሆይ በሙዚቃ ጠበብቶች ሲዘከሩ... እማሆይ አራቱን የኢትዮጵያ ቅኝቶች በአንድ ድርሰት በመቀመማቸው የሙዚቃ ጠበብት ያደንቋቸዋል። ከሰሞኑ "የፒያኖዋ እመቤት" እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ በሕይወት ዘመናቸው ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ኢንዱስትሪ ዕድገት የነበራቸውን አበርክቶ የሚዘክር መርሐግብር በእንጦጦ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ ሲካሄድ በርካታ ታዋቂ ሰዎችና የኪነ ጥበብ ሰዎች ታድመው ነበር። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እማሆይ ጽጌማርያም በጠላት ወረራ የአርበኝነት ዘመን ክፉውን ጊዜ የቀመሱ፣ ሕይወታቸውም አልጋ ባልጋ ሳይሆን በውጣ ውረድ የተሞላ፣ በሀገር አንድነትና በኅይማኖት በጽኑ የሚያምኑ እንደሆኑ ገልጸዋል። "የሙዚቃ ስራዎቻቸው ፍትህን፣ አንድነትን፣ መንፈሳዊነትን እና ሰላምን የሚገልጹ ናቸው። የእማሆይ የሙዚቃ ስራ በተጨነቅን ጊዜ ስናደምጥው መንፈስ የሚያረጋጋ ሕያው ስራ ነው፤ ተማሪዎች ፈለጋቸውን እንደሚከተሉ ተስፋ አደርጋለሁ" ሲሉ ተደምጠዋል።   የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሰብሳቢ አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ "የእማሆይ ጽጌማርያም ስራ በወረቀት ተጽፎ የሚቀር ሳይሆን በልብና በአዕምሯችን ታትሞ የሚቀር ነው" ሲሉ ገልጸውታል። በረቂቅ ሙዚቃ አጨዋውታቸው ዓለምን ያስደነቁ፤ የህያው ስራ ባለቤት እንደሆኑም እንዲሁ። በእንጦጦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሙዚቃ ባለሙያው በላይ አለማየሁ እማሆይ ጽጌማርያም "ዘመናዊ ሙዚቃ ባልተለመደበት ዘመን አዲስ የሙዚቃ ስነ ዘዴ ያመጡ፤ የሙዚቃ ስራዎቻቸውም ኢትዮጵያዊውን ቃና ከአውሮፓ ሙዚቃ በማዋሀድ በሁለት ቅኝቶች ውህደት አዲስ ፈጠራ ያመጡ፣ የሙዚቃ ዕውቀታቸው የሚያስደንቅ፣ ዋጋ ከፍሎ ህልምና ማሳካት እንደሚቻል በሙዚቃ ልህቀት ላይ በመድረስ በተግባር ያሳዩ የጥበብ ሰው፣ ለሙዚቃው ዘርፍ ተግባራዊ ምሳሌ ናቸው" በማለት ይገልጸዋቸዋል። የሙዚቃ ትምህርት ክፍል አሰልጣኟ ዊንታና ንጉሴ በበኩሏ "እማሆይ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ትልቅ ሚና የተጫወቱ ስራዎቻቸውም የሚዘከሩ ናቸው፤ እንደ ሙዚቃ መምህርነቴም አርዓያዬ ናቸው" ትላለች። በእማሆይ ጽጌማርያም ስራዎች ላይ የመመረቂያ ስራዋን ያዘጋጀቸው ሰዓሊና ዲዛይነር ሀበሪ እጅጉ በበኩሏ "እማሆይ ምድራዊና ሰማያዊ ሕይወት አቻችለው የኖሩ፤ ሁለት ድል ያሳዩ ናቸው። ጥቁር ኢትዮጵያዊ ሆነው በዓለም የታወቁ፣ ለዓላማችው ስኬት ትልቅ ተጋድሎ ያደረጉ፣ በመክሊት መኖርን የሚያስተምሩ እናት" ትላቸዋለች። የኢትዮ ጃዝ አባት የሚሰኘው አንጋፋው ሙዚቀኛ ሙላቱ አስታጥቄ ከወራት በፊት ለቢቢሲ በሰጠው ቃለ መጠይቅ "እማሆይ በእውነት እጅግ የማደንቃቸው እና የማከብራቸው ታላቅ ባለሞያም፤ ታላቅ ሰው ናቸው። ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል.... የእማሆይ ጽጌ ማርያም ሥራ ተጠንቶ በየትምህርት ቤቱ እንዲቀመጥ፣ እንዲጠና ማድረግ የግድ አስፈላጊ ነው ብዬ አምናለሁ። የሙዚቃ ትምህርት ካሪኩለም ውስጥ እንዲገባ እና ወጣቶቹ እንዲማሩት ማድረግ ያስፈልጋል" ይላል። ዕውቁ የሙዚቃ ባለሙያ ሃያሲ ሰርፀ ፍሬስብሃት በአንድ ወቅት በፃፈው መጣጠፍ እማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩ በክላሲካል ሙዚቃ ዘርፍ በብቸኛ የሙዚቃ ቀማሪነት እና ፒያኒስትነት ጉልህ የታሪክ ቦታ እንደያዙ ገልጿል። "እማሆይ ጽጌ ማርያም በሙዚቃ ምክንያት ብዙ ተፈትነዋል፡፡ ከመንፈሳዊ ሕይታቸው ጋር የሚቃረን የሚመስላቸው አንዳንዶች፣ ሙያቸውን እና የሙዚቃ ፍቅራቸውን አጣጥለውባቸዋል፡፡ የሕይወታቸውን አቅጣጫ ፍጹም በማይገመት መንገድ እንዲጓዝ ያደረገም ነው፡፡ ከሀገራቸው አሰድዶ ተነጥለው እንዲኖሩ ያደረገ ነው፡፡ ግን ከዚህ ኹሉ በኋላ የስማቸው ትንሣኤ፣ ከዘጠኝ ዐሥርት ዓመታት በኋላ በታላቅ ክብር ለብዙዎች ታይቷል" ብሏል፡፡ እማሆይ ራሳቸውም "አንዳንድ ሰዎች ይቃወሙታል። ነገር ግን ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው የሚሆነው። ይሄ የክላሲካል ሙዚቃ ነው። እግዚአብሔርንም በተለያዩ የሙዚቃ መሳሪያዎች ማወደስ ይቻላል" ሲሉ ለቢቢሲ ራዲዮ ፎር ተናግረዋል። ሰሞን ታዋቂው ጋዜጣ ኒወርክ ታይምስ "ባለልዩ ተስጥኦ ኢትዮጵያዊ መነኩሲት" በሚል ሰፊ ሀተታ ጽፏል። በዚሁ ጋዜጣ ላይ ኖራ ጆንስ የተባለ ሙዚቀኛ "የእማሆይ አልበም እስካሁን ከሰማኋቸው ውብ ሙዚቃዎች ሁሉ የላቀ ስራ ነው" ሲል አድንቆታል። እስራኤላዊት ሙዚቀኛ ማያ ዱኔትዝ እማሆይ "የምዕራቡን ዓለም ረቂቅ ሙዚቃ ከኢትዮጵያዊ ባህላዊ ሙዚቃ ቅርስ ጋር በመቀመር ለዓለም ጆሮ አዲስ ድምጽ አፍልቀዋል። …ሙዚቃዎቻቸው በስፋት መንፈሳዊ መልክ አላቸው። የእማሆይ ሙዚቃዎች የጥሞና፣ ትህትና፣ የጥልቅ ተመስጦ፣ የሰላማዊ ድባብ፣ አሳዛኝ ግን በፍቅርና በእምነት የተዋጡ ... ድምጾች" በሚል ትገልጻቸዋለች። እማሆይ ጽጌማርያም የሙዚቃ ኅይል በርግጥም ውስጥን የሚፈነቅል፤ መንፈስን የሚሰረስር መሆኑን በዘመናቸው ሁሉ ከሙዚቃ ጋር ላይነጣጠል ከህይወታቸው የተጋመደ በሰሯቸው ዘመን አይሽሬ ስራዎች አሳይተውናል። የእማሆይ ጽጌማርያም የአንድ ምዕተ ዓመት ምድራዊ ሕይወት ዘላለማዊ አይረሴ ስራዎች በትውልዱ ውስጥ እንደረቀቁ ይኖራሉ።  
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች
May 26, 2023 210
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች ሰለሞን ተሰራ አውሮፓዊያን ለጥቁሮች ከነበራቸው ዝቅተኛ አመለካከት በመነጨ እብሪት “የአፍሪካ ቅርምት” እየተባለ በሚታወቀው አጀንዳቸው አህጉሪቱን ለመከፋፈል ቁጭ ብለው የመከሩት በ18ኛው ክፍለ ዘመን ማገባደጃ ላይ ነበር፡፡ በጀርመን መዲና በርሊን የተሰበሰቡት ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ፖርቱጋል፣ ቤልጂየም እንዲሁም ዘግይተው የተቀላቀሉት ጣልያን እና ጀርመን አቅማቸው የፈቀደውን ያህል አህጉሪቱን በመቆጣጠር ሀብቷን ለመመዝበር ሕልም አንግበው የወል ቃል ገብተዋል፡፡ እነዚህ ሀገራት አፍሪካን አንድ አድርጎ ለመግዛት ሕልማቸውን አስተሳስረው ቢነሱም በመሀከላቸው በነበረው ፉክክር የተነሳ ምኞታቸው ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡ አውሮፓውያን በአህጉሪቱ የዘረጉትን የቅኝ አገዛዝ መዋቅር በጣጥሶ ለመጣል በቅድሚያ አህጉሪቱን አንድ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን የሚያምኑ አፍሪካውያን መሪዎች ህብረት ለመመስረት ቢነሱም ሀሳባቸው ለሁለት በመከፈሉ ሁለት ቡድን እንዲፈጠር ምክንያት ሆኖ አልፏል፡፡ ይህን ተከትሎ የተፈጠሩት ሁለት ቡድኖች በአንድ ወገን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ሀገራቱ በፍጥነት ተዋሕደው አፍሪካ አንድ ልትሆን ይገባል የሚለው የካዛብላንካ ቡድን፤ እንዲሁም አንድ ከመሆን በፊት ሌሎች ትብብሮች ሊቀድሙ ይገባል የሚለው የሞኖሮቪያ ቡድኖች ነበሩ፡፡ ሁለቱም ቡድኖች የአፍሪካ አንድነት እንዲመሰረት ጽኑ አቋም ቢኖራቸውም፣ እንዴት ነው መመስረት ያለበት የሚለው ጥያቄ ግን የልዩነታቸው ወሰን ሆኖ ወደ ንትርክ የገቡበት ጊዜ ነበር። በ1961 የተመሰረተው የካዛብላንካው ቡድን በጋናዊው ኩዋሜ ኑኩርማህ የሚመራ ሲሆን ዓላማቸው አፍሪካ አሁን መዋሃድ (አንድ መሆን) አለባት የሚል ሲሆን ከአባላቱ መካከል ጊኒ፣ ሊቢያ፣ ግብጽ፣ ሞሮኮ፣ ማሊ፣ አልጄሪያ ይገኙበታል። የሞኖሮቪያው ቡድን ደግሞ በሴኔጋላዊው መሪ ሴንጎር የሚመራ ሲሆን በስሩም ሃያ አራት ሃገራትን፣ ማለትም ናይጄሪያ፣ ሴኔጋል፣ ካሜሮን፣ አይቮሪኮስት፣ ቶጎ፣ ላይቤሪያ እና ሌሎች ብዙ የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበሩ ሃገራትን ያቀፈ ነበር፡፡ የዚህ ቡድን የውህደት መርህ ደግሞ “አፍሪካ መዋሃድ የምትችለው በኢኮኖሚያዊ ትብብር ሆኖ በቀስታ በምታደርገው ጉዞ ነው” የሚል ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ወገኖች ፍጥጫ አርግባ ወደ ውህደት ያመጣቻቸው ኢትዮጵያ ስትሆን ድርጅቱ የዛሬ 60 ዓመት እ.ኤ.አ ግንቦት 25 ቀን 1963 ሲመሰረት የመጀመሪያው ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት አጼ ኃይለስላሴ ነበሩ፡፡ የፓን አፍሪካኒዝም ልጅ የሆነው የያኔው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋና ዋና ዓላማዎቹ ቅኝ ገዢዎችን ማስወገድ፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል አንድነትና ሕብረትን ማበረታታት፣ ለአፍሪካዊያን የተሻለ ህይዎት እና እድገት ለማምጣት፣ ሉዓላዊነትንና የወሰን አንድነትን ማስጠበቅ፣ ሰብዓዊ መብቶችን ማስከበር፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል የሚካሄዱትን ግጭቶች በሰላማዊና በዲፕሎማሲ መፍታት የሚሉ ነበሩ። የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀደምት መሪዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን የሚተካ አዲስ አህጉራዊ ድርጅት ለመመስረት እ.አ.አ በ1999 ያሳለፉትን ውሳኔ መሠረት በማድረግ የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ በሐምሌ 2002 በደርባን ደቡብ አፍሪካ በይፋ መመስረቱ ይታወቃል። የአፍሪካ ኅብረት ራዕይም፤ የተቀናጀች፣ የበለጸገች እና ሰላማዊ፣ በራሷ ዜጎች የምትመራ እና በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ተፎካካሪ የሆነች አፍሪካን መመስረት ነው። እ.አ.አ በ2013 የአፍሪካ መሪዎች በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት አጀንዳ 2063 የተሰኘውን አህጉራዊ እቅድ ነድፈዋል። እቅዱ ከሁሉም በላይ በአህጉሪቱ ላይ የሚቃጡ ጦርነቶችን ማስቆምና መሰረተ ልማት ዝርጋታ ላይ የሚያተኩር ሲሆን በአህጉሪቱ ዜጎች ከአገር አገር ነፃ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ራዕይ የሰነቀ ነው። ሌላው ወሳኝ ፕሮጀክት የአፍሪካ ነፃ ገበያ ምህዳርን መክፈት ሲሆን ይህ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ በርካታ አገራትን አሳታፊ በማድረግ የዓለም ትልቁ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ ስምምነት ሲሆን አሁን ላይ ተግባራዊ ሊደረግ ከጫፍ ደርሷል። ይህ የነፃ ገበያ ስምምነት በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ለማስፋፋት የታለመ ከመሆኑ በላይ የሀገራቱን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድገው ታምኖበታል። የአፍሪካ ነፃ ገበያ ስምምነት አገራት የውስጥ ገበያቸውን ለመጠበቅ ባወጧቸው ቀደምት ህጎችና እንዲሁም በደካማ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ምክንያት ከፍተኛ ችግር እንደሚገጥመው አስተያየት ቢሰጥበትም ያዘለው ተስፋ ግን ከችግሩ የገዘፈ ነው። ሁሉንም የአፍሪካ አገራት መዲናዎች እና የንግድ ማዕከሎች በፈጣን የባቡር መስመር ማገናኘት፣ በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ማበረታታት እንዲሁም የአፍሪካ አገራት በዓለም አቀፍ የንግድ ገበያ ያላቸውን ተሳትፎ ማጎልበት አጀንዳ 2063 ካስቀመጣቸው ግቦች መካከል ቀዳሚዎቹ ናቸው። አፍሪካውያን በአህጉሪቱ በነፃነት የመዘዋወር፣ የመስራት እና የመኖር መብት እንዲኖራቸው ማድረግ እንዲሁም በአህጉሪቱ ያሉ ግጭቶችን ማስቆም እና ሌሎችም በርካታ ግቦች በእቅዱ ላይ ተቀምጠዋል። ነገር ግን የአፍሪካ ሕብረት እነዚህን አጀንዳዎች ለማስፈፀም በእጅጉ እየተፈተነ ሲሆን ለዚህ ዋነኛ መንስኤው የሕብረቱ አባል አገራት በገቡት ስምምነት መሰረት ነገሮችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ማስገደድ አለመቻሉ እንደሆነ ይነገራል። ተንታኞች እንደሚሉት የአፍሪካ አገራት ያለባቸውን ከፍተኛ የእዳ ጫና ለመክፈል የሚያደርጉት ትግል ትልቁን አህጉራዊ አጀንዳ ችላ እንዲሉ ግድ ብሏቸዋል። የህብረቱ በጎ ርምጃዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋነኛ ዓላማው በቅኝ አገዛዝ ስር የነበሩ ሀገሮችን ነጻ ማውጣት ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር የተሳካ ተግባር ማከናወኑ በታሪክ ሲወደስለት የሚኖር ስኬቱ ነው፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆኖ ከሞላ ጎደል ውጤት ያስመዘገበባቸው ዘርፎች አሉ። ሀ. ሰላምና ደህንነት የአፍሪካ ህብረት ሰላምንና ደህንነትን ለማረጋገጥ በተለይም የአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ኃይል በተለያዩ የአህጉሪቱ ክፍሎች ያደረገው ተጋድሎ በአዎንታ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ ለማሳያም ላይቤሪያ፣ ሴራሊዮን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን ተሰማርቶ የነበረው የአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ኃይል ከሌሎች የተሻለ አፈጻጸም እንዳለው ይገለጻል፡፡ ለ. ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በተለያዩ የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መረጋጋት እንዲፈጠር ለማድረግና ዴሞክራሲን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት እና የተፈጥሮ ሃብቷ ለፈጣን ዕድገቱ በምክንያትነት ይነሳሉ፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋና ኢኮኖሚው እንዲያድግ የወሰዳቸው ተቋማዊ እርምጃዎች ወሳኝ ሚና ሲኖራቸው የአፍሪካ ልማት ባንክን በማቋቋም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መደገፉ ተጠቃሽ ነው፡፡ በተለይም ለመንገድና ለውኃ ሃይል ማመንጫ ባንኩ ያደረገው ድጋፍ ተገቢው ቦታ የሚሰጠው ሲሆን ለአፍሪካ የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነት መሻሻል ማነቆ የሆኑትን ታሪፍ በመቀነስም የተሻለ ስራ ሰርቷል፡፡ ሐ. ዓለም አቀፍ ተሰሚነት የአፍሪካ ህብረት በዓለም አቀፍ መድረኮች በተለይም የዓለም ኢኮኖሚንና የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከተ አንድ አቋም መያዙ ከህብረቱ ታሪክ ተጠቃሽ ስኬቶች አንዱ ነው፡፡ አፍሪካ የአየር ንብረት ተፅዕኖውን ለመላመድና ለመቋቋም የሚረዳትን ተገቢውን ክፍያ እንድታገኝ ህብረቱ ውጤታማ ስራ ሰርቷል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ የልማት ችግሮችን ለመፍታት ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ጥረት አድርጎ ባስመዘገበው ውጤትም ይመሰገናል፡፡ በተለይም የተባበሩት መንግስታት የሚሊኒየም የልማት ግቦች እንደ መገለጫ ይነሳሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ለማግኘት እንዲሁም የአፍሪካ ድምጽ የሚጎላበት ሚዲያ እንዲኖር የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች በአዎንታ የሚነሱ ናቸው። መ. ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ ዴሞክራሲንና መልካም አስተዳደርን በማስፈን በኩልም ከነጉድለቶቹም ቢሆን በመልካምነት የሚጠቀሱ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይገለጻል፡፡ በአህጉሪቷ ከ30 ዓመት በፊት አምስት ሀገራት ብቻ ዴሞክራት የነበሩ ሲሆን አሁን ከአፍሪካ ሀገሮች 95 በመቶዎቹ ወቅቱን ጠብቀው ምርጫ የሚያካሂዱ ሀገራት ናቸው፡፡ የምርጫ ታዛቢዎችን በአባል ሀገራት እየላከ መታዘቡም እንደ ጥሩ ጅምር መታየት ያለበት ነው፡፡ በተለይ ደግሞ የአፍሪካ የእርስ በርስ መገማገሚያ መድረክን /APRM/ ማቋቋሙ በጥንካሬ ሲነሳ በዚህ መድረክ አማካኝነት ሀገራት በራሳቸው ተነሳሽነት ስለሀገራቸው የመልካም አስተዳደር አፈጻጻም ሪፖርት የሚያደርጉበትና ልምድ የሚለዋወጡበት እድል ተፈጥሯል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በሀገሮች ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ያለመግባት መርህ በማሻሻል በመፈንቅለ መንግስት የሚመጡ ቡድኖችን ላለመቀበል መወሰኑ ህብረቱ በዴሞክራሲ ላይ ያለውን አቋም ያሳያል፡፡ መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች በርግጥ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት አንግቦት ከነበረው አባል ሀገራቱን ከቅኝ ገዥዎች ነፃ የማውጣት ተልዕኮ አንስቶ እስከ ወቅታዊው የአየር ንብረት ለውጥ ድርድር አበጀህ የሚያስብሉትን ስኬቶች አስመዝግቧል፡፡ በቀዝቃዛው የዓለም ጦርነት ጊዜ አብዛኛው ሃገራት የገለልተኛ ሀገሮች ማህበር አባል ቢሆኑም የአፍሪካ ሀገሮች እርስ በእርሳቸው ተከፋፍለው አፍሪካን የጦርነት አውድማ አድርገዋት ነበር፡፡ አንዱ የአፍሪካ ሀገር የምዕራቡ ካምፕ ደጋፊ ከሆነ ሌላኛው የምስራቅ ካምፕ ደጋፊ ነበር፡፡ ሁለቱም ካምፖች ለርዕዮተ ዓለም ተከታዮቻቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ በማድረግ አፍሪካ እርስ በእርስ እንድትባላ አድርገዋል፡፡ ይህም ህብረቱ የተቀደሰ ሃሳብ ቢኖረውም የማስፈፀም አቅሙ ያን ያህል የተጠናከረ አለመሆኑን ያሳያል፡፡ ለህብረቱ የማስፈጸም አቅም ማነስ አንደኛው ምክንያት ከአባል ሀገራት የሚጠበቀውን ገንዘብ በአግባቡ አለመሰብሰቡ ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የህብረቱ የ2023 በጀት 654 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር እንዲሆን በዛምቢያ በተደረገ ጉባኤ ውሳኔ የተላለፈ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 60 በመቶ የሚልቀው በጀት ከለጋሾች እንደሚሰበሰብ በወቅቱ ይፋ ተደርጓል፡፡ በሌላ በኩል አፍሪካ በየዓመቱ 50 ቢሊዮን ዶላር በሙስና እንደምታጣ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ 1 በመቶ እንኳን ማዳን ቢቻል የህብረቱን የ2 ዓመት ወጪ መሸፈን ይቻላል ይላሉ ባለሙያዎች፡፡ ጥቂት በማይባሉ የህብረቱ አባል ሀገራት ሙስና ዛሬም አደጋ መሆኑ፣ የርስ በርስ ግጭት በሚፈለገው ደረጃ አለመፈታቱ፣ ድህነት አሁንም የአህጉሪቱ ቀንደኛ ጠላት መሆኑ፣ የትምህርትና ጤና አገልግሎቶች ተደራሽ አለመሆንና ጥራቱም የተጓደለ መሆን፣ በህብረቱ የሚወሰኑ ውሳኔዎች አፈጻጸም የተለያየና የሚፈለገውን ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ ውስንነት ያለበት መሆኑ ወዘተ የህብረቱና አባል ሀገራት ጉድለት ሆነው ቀጥለዋል። ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች የአፍሪካ ህብረት ከስኬቱም ሆነ ከልምዱ ለመማር የሚያስችለው ከግማሽ ክፍለ ዘመን የዘለቀ የእድሜ ባለፀጋ ሆኗል፡፡ እናም የወደፊት አቅጣጫውን ሲተልም ያለፈውን ጉዞ ዞር ብሎ ማየት፤ የቆመበትን ነባራዊ ሁኔታ ጠንቅቆ መረዳትና መጭውን አቅርቦ ማሰብ ይጠበቅበታል። ለዚህ ደግሞ የማስፈጸም አቅምን ማጠናከር፣ ለስራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት መስጠት፣ ተሳትፎን ማሳደግ፣ የገቢ አቅምን ማሳደግ ወሳኝ ናቸው። ሀ. የማስፈጸም አቅም የአፍረካ ህብረት ከአፍሪካ አንድነት ደርጅት የተሻለ አደረጃጀትና አሰራር እንዳለው የሚቀበሉ አሉ፡፡ ለምሳሌ በሀገሮች ጣልቃ ያለመግባት መርህን በማሻሻል ህብረቱ በመፈንቅለ መንግስት የመጡ ቡድኖችን በአባልነት አይቀበልም ነገር ግን በአፍሪካ አሁንም የእርስ በርስ ግጭት የሚታይባቸው ሀገሮች አሉ፡፡ ስለሆነም ይህንኑ ችግር ሊቀርፍ የሚችልና ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበ አደረጃጀትና አሰራር ሊኖረው ይገባል፡፡ የህብረቱ በጀት በሌሎች አካል መሸፈን አሉታዊ ተፅዕኖ ስለሚኖረው አባል ሃገራት የሚጠበቅባቸውን መዋጮ በወቅቱ በመክፈል የህብረቱን የማስፈፀም አቅም ማሳደግም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለ. የስራ እድል ፈጠራ የአፍሪካ ህብረት በተለይ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ማዕከል ያደረገ እድገትን ማበረታታት ግድ የሚለው ወቅት አሁን ነው፡፡ ሆኖም ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ከማረጋገጥ አኳያ ብዙ የሚቀሩ ስራዎች እንዳሉ እሙን ነው። በተለይም ወጣቶችን ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ መሰራት ያለባቸው የቤት ስራዎች በአግባቡ አለመሰራታቸው በጉልህ ይጠቀሳሉ፡፡ እንደ አፍሪካ ኢኮኖሚ አውትሉክ መረጃ በአፍሪካ እድሜያቸው ከ15 እስከ 25 ዓመት ያሉ ወጣቶች ከአህጉሪቱ አጠቃላይ ህዝብ ከ70 ከመቶ በላይ ይሸፍናሉ፡፡ የዓለም ባንክ ያወጣው መረጃ እንደሚያሳየው በአፍሪካ 200 ሚሊዮን የሚጠጉ እድሜአቸው ከ15 እስከ 25 የሚጠጋ ወጣቶች ሲኖሩ ከነዚህ መካከል 60 በመቶ የሚጠጉት ስራ ፈላጊ መሆናቸው ደግሞ ህብረቱ የሚጠብቀውን ከባድ ስራ ያሳያል፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በየሃገሮቹ ለወጣቶች ምን ያህል የስራ እድል እንደተፈጠረ መጠየቅን የእርስ በእርስ መገማገሚያ መድረኩ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ ሊያደርገው እንደሚገባ ምሁራን ይመክራሉ፡፡ ሐ. የህዝብ ተሳትፎና የውክልና ዴሞክራሲ ህብረቱ ሊያሳካ ያሰባቸውን ግቦች እውን ማድረግ የሚቻለው በሁሉም የነቃ ተሳትፎ መሆኑ አያጠያይቅም። በመሆኑም አባል አገራት ችግሮችን ከመለየት ጀምሮ እስከ ክትትልና ግምገማ ስርአት ህብረተሰቡን በሁለንተናዊ መርሃ ግብሮች ማሳተፍ ይገባቸዋል፡፡ ይህ ሲደረግ ነው በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ ያሉ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የፈጠራ ችሎታዎችን ማውጣትና ሀገሬ ለእኔ ምን አድርጋለች ሳይሆን እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ የሚሉ ዜጎችን መፍጠር የሚቻለው፡፡ በአፍሪካ በየቦታው የሚታዩ የእርስ በእርስ ግጭቶች መንስኤ በዋነኛነት የህዝብ ፍላጎት አለመሟላት ሲሆን በተለይም የአናሳዎች መብት አለመከበር የግጭት መንስኤ ሲሆን ይታያል፡፡ ለዚህ ደግሞ በየአካባቢው አስተዳደር ህዝቡን በየጊዜው ማማከር ያስፈልጋል፡፡ መ. ውስጣዊ የገቢ አቅምን ማሳደግ በዋናነት አራት የገቢ ምንጮች ያሉ ሲሆን እነሱም የሃገር ውስጥ ብድር፤ ግብርና ታክስ፣ የውጭ ብድር እና እርዳታ ናቸው፡፡ ከግብርና ታክስ በስተቀር ሌሎች የገቢ ምንጮች አሉታዊ ተጽዕኗቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ግብርና ታክስን በአግባቡ መሰብሰብ የአንድ ሀገር የሁለንተናዊ ብቃት መለኪያ ነው፡፡ ግብርና ታክስ የመንግስት ወጪ በመሸፈን ነጻነትን ከማጎናጸፉም በተጨማሪ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍልን ለማረጋገጥ ሁነኛ መሳሪያ ነው፡፡ አልጀዚራ ባወጣው መረጃ መሰረት አፍሪካ በእርዳታና በብድር ከምታገኘው ይልቅ በታክስ ማጭበርበርና ስወራ የምታጣው ከ10 እጥፍ በላይ ይበልጣል፡፡ ለዚህ ደግሞ የታክስ ህጎች ክፍተት መኖርና በሙስና የተጨማለቁ ባለስልጣናት እንዲሁም ብቃት ያለው የሰው ኃይል አለመኖር አስተዋፆኦ ያደርጋሉ፡፡ የገቢ አሰባሰብ ስርአቱን በማሻሻል የአፍሪካን ነጻነት ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአፍሪካን የእርስ በርስ ንግድ ማስፋፋት፤ የታሪፍና ቀረጥ ምጣኔን ማሻሻል፤ የወጪ ገበያ የምርት አይነቶችን ማስፋትና ሃገራቱን በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር የየሃገራቱን የተናጠል ጥረትና የህብረቱን አመራሮች የጋራ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራቱን በማስተባበር ባለፉት 60 ዓመታት ያለፈበትን የውጣ ውረድ ጉዞ በማጤን የተሻለ ነገን ለመገንባትና የአፍሪካን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከትላንቱ በበለጠ መትጋት ይገባዋል።      
"እንሰትና ሁለገብ ጠቀሜታው"
May 6, 2023 1163
በፍሬዘር ጌታቸው እንሰት በኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ያስቆጠረ፤ በተለይ በደቡቡ የሀገሪቱ ክፍሎች በስፋት የሚመረት ተክል እንደሆነ የታሪክ ድርሳናትና በዘርፉ የተካሄዱ ጥናቶች ያስረዳሉ። እንሰት በደቡብ የሀገራችን ክፍል በሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝብች ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ነውና የምግብ ዋስትና አለኝታ ተደርጎ የሚወሰድ ተክል ነው። ተፍቆ ለምግብነት ወሳኝ የጤንነት መጠበቂያና የጥንካሬ መሰረት ተደርጎ ይወሰዳል። የእንሰት ተክል የሚጣል ነገር የለውም። ተረፈ ምርቱ ለእንሰሳት መኖ ጭምር ያለው ፋይዳ የላቀ ነው። እያንዳንዱ የእንሰት ተክል ክፍል ከምግብነት ባሻገር ለተለያዩ አገልግሎቶች ይውላል። የእንሰት ተክል ለም አፈር በንፋስና በጎርፍ ታጥቦ እንዳይወሰድ የመከላከል አቅሙ ከፍተኛ ነው። ከዚህም ባሻገር የአፈር ለምነትን እና እርጥበት ጠብቆ በማቆየት ለምርታማነት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው በመሆኑ ከደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች ሕዝቦች ጋር ያለውን ቁርኝት ዘመን ተሻጋሪ ያደርገዋል። ለአብነትም እንሰት በወላይታ ብሄር ከሰውና ከእንስሳት ምግብነት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን በአካባቢው "ኡታ" ተብሎ ይጠራል። እንሰት ወይም "ኡታ" የባለፀጋነት መገለጫም ነው። የመኖሪያ ቤቱን ዙሪያ፣ ቀዬውን በእንሰት የከለለና ያስዋበ፣ ማሳውን በእንሰት ያለማ አባወራ ባለጠጋ እንደሆነ ይታመናል። አባወራውም "አላ ኡታ ጎዳው" በማለት ይሞካሻል። እንሰት ለምግብነት፣ ለመደኃኒትነት፣ ለአካባቢ ውበት፣ ለአፈር እርጥበትና ለምነት ለመጠበቅ፣ ለእንሰሳት መኖነት፣ ለባህላዊ ቤት ስራ ጣራና ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት ያገለግላል። እንዲሁም ኮባው (ቅጠሉ) እንደ ዳቦ ለመሳሰሉት ምግብ ማብሰያና ለተለያዩ የግብርና ዉጤቶች መጠቅለያነት ግልጋሎት ይውላል። ከእንሰት ተረፈ ምርቶች የመቀመጫና የወለል ምንጣፎችን ጨምሮ በርካታ መገልገያዎች ይሰራሉ። የእንሰት ተክል በተለያዩ አካባቢያዊ ሁኔታ መብቀል ከመቻሉ ባሻገር ድርቅን የመቋቋም አቅሙ ከፍተኛ ነው። በዚህም አካባቢው ላይ ድርቅ በተከሰትበት ወቅት "ነፍስ አድን" የሚል ስያሜም ተሰጥቶት እንደነበር በታሪክ ይናገራል። የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር መለሰ መኮንን እንሰት ምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥና የልማት ችግሮችን ከማቃለል አንጻር ከፍተኛ ሚና ያለው ነው ይላሉ። ተክሉ በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብና በሲዳማ ክልሎች በስፋት እንደሚለማና በሀገሪቱ ከ3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በላይ በተለያየ የእንሰት ዝርያ መሸፈኑን ያስረዳሉ። ከሀገሪቱ ህዝቦች ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የእንሰት ተዋፅኦን የሚመገቡና የሚገለገሉ ናቸው። የእንሰት ተክል በባህሪው የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም የከፍተኛ አቅም ያለው በመሆኑ፤ ለዝናብ እጥረትና ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ተክሉን በስፋት በማልማት የምግብና ዋስትናን በዘላቂነት ማረጋገጥ ይቻላል ይላሉ። እንሰትን ለምግብነት ከመጠቀም ባሻገር ለገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ ሀብት በመሆኑ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የተሻለ አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ጥረት ማድረግ ይጠይቃል ሲሉ ያስረዳሉ ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር መለሰ። እንሰት በአካባቢው ማስገኘት ከሚገባው ጠቀሜታ አንፃር ሲታይ እየሰጠ ያለው ጥቅም ከአቅም በታች ነው የሚሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የእንሰት ሰብል ተመራማሪ ዶክተር አብርሃም ቦሻ ናቸው። በመሆኑም የእንሰትን ምርታማነት ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲው የምርምር፤ የማህበረሰብ አገልግሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን በትኩረት እየሰራ ነው ይላሉ። በኢትዮጵያ ከባህር ጠለል በላይ ከ1 ሺህ 500 እስከ 3 ሺህ 100 ሜትር ከፍታና አማካይ የዓመት ዝናብ መጠን ያለው አካባቢ ለእንሰት ተክል ምቹ ሲሆን፤ እንሰት ዝናብን የሚተካ አማራጭ የውሃ ምንጮች ባሉበት አካባቢ ከ1 ሺህ 500 ሜትር በታች በሆኑ ቆላማ አካባቢዎችም ምርት ሊያስገኝ ይችላል ይላሉ። እንደ ተመራማሪው ገለጻ እንሰት በሀገሪቱ ከሚገኙና ዋና ዋና ሰብሎች ከሚባሉት መካከል አንዱና ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው ነው። ተክሉ ተራራማ ቦታዎች ላይ ጭምር በምቾት የሚያድግ ሲሆን እንደ ዝርያው ዓይነት ከሶስት እስከ አምስት ዓመት ውስጥ ምርቱ ውጤታማ መሆን ይችላል። ዝርያው "ወንዴ" እና "ሴቴ" ተብሎ የሚከፈል ሲሆን፤ 60 ያህል የእንሰት ዝርያዎች አሉ። ከምርት አያያዝና ብቃት አንጻር ሲታይ ከእያንዳንዱ የእንሰት ተክል ከ40 ኪሎ በላይ ዱቄት ይገኝበታል። እንሰት ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ጉልህ አስተዋፅኦ ያለው ሰብል ነው፤ ከዛም አልፎ ለሰውና ለእንስሳት ከተለያየ በሽታ የመከላከልና ከጉዳት ለማገገም የሚያስችል መድኃኒት ነው። ተክሉን የማባዛት ስራ በባህላዊ መንገድ የሚከወን ሲሆን፤ የእንስሳትና ሌሎች የሚወገዱ ተረፈ ምርቶችን በመጨመር እድገቱን ውጤታማ ማድረግ ይቻላል። ከእንሰት ምርት የሚገኘው ዱቄት ቡላ ወይም በአካባቢው አጠራር "ኢቲማ" ለልጆችና ለአዋቂዎች ጤና ተስማሚ ሲሆን፣ ገንፎ፤ የክትፎ የአይብና ጎመን ማባያ ቆጮ "ኡንጫ" እንዲሁም ሙቾና ባጭራ ለምግብነት ከሚውሉት ተጠቃሽ ናቸው። የእንሰት ተክል በተለያዩ የአፈር ዓይነቶች ላይ የሚለማ፣ የአየር ንብረት ለውጡን የመቋቋም አቅም ያለው ተክል ነው። የወላይታ ዞን እንሰት አብቃይ ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ ሲሆን በተለይም በባይራ ኮይሻ፣ በቦሎሶ ሶሬና በአንዳንድ የሶዶ ዙሪያ ወረዳዎች በተደረገ የዳሰሳ ጥናት የእንሰት ተክል የመመናመንና የበሽታ አደጋ እንደተጋረጠበት ዶክተር አብርሃም አብራርተዋል። ለዚህም ምርቱን መልሶ ለማስፋፋትና ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ከዞኑ ግብርና መምሪያ ጋር በመሆን በትብብር እየተሰራ መሆኑን ያስረዳሉ። የወላይታ ዞን የግብርና መምሪያ እርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ዓለሙ እንዳሉት በወላይታ ዞን ከ28 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በእንሰት ተክል የተሸፈነ ነው። የእንሰት ተክል የሚፈለገውን ምርትና ውጤት እንዳይሰጥ ከሚያደርጉ ተግዳሮቶች መካከል ዋነኞቹ የአጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ፣ የተለያዩ ተባዮች፣ ፍልፈልና ጃርት ይጠቀሳሉ። የእንሰት አጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ በሁሉም የእንሰት አብቃይ ስነ-ምህዳር የሚገኝ፣ በሁሉም የእድገት ደረጃ ላይ ያለን የእንሰት የሚያጠቃና ከአንዱ ወደ ሌላው ተክል የሚተላለፍ መሆኑ ችግሩን የከፋ ያደርገዋል። በመሆኑም ችግሩን ለማስወገድ ጤነኛ የእንሰት ተክሎችን በላቦራቶሪ የማባዛት፣ የበሽታ አምጪ ተህዋሲያን የማጥናትና በጄኔትክ ምህንድስና በሽታን የሚቋቋም ቅንጣት ወደ እንሰት የማስገባት ሥራ እየተሰራ ነው። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣ ከሶዶ ግብርና ኮሌጅ እንዲሁም ከአረካ የምርምር ማዕከል ጋር በመሆን በጋራ እየተሰራ ነው። ኃላፊው እንዳስረዱት ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በሽታን የሚቋቋሙ ከ20 ሚሊዮን በላይ የእንሰት ችግኞችን አባዝቶ በመትከል የተሻለ ውጤት እየታየ ነው። ይህን ሥራ በማጠናከር ከእንሰት ዘርፍ ሊገኝ የሚገባውን ጥቅም ለማግኘት አርሶ አደሩ ያለውን አገር በቀል ዕውቀቱን በአግባቡ እንዲጠቀም በከፍተኛ ንቅናቄ እየተሰራ ይገኛል። በዚህም የአካባቢውን የእንሰት ሽፋን ማሳደግ ብቻ ሳይሆን የአርሶ አደሩን ጥያቄ መመለስና ጥቅሙን ለማላቅ የተጀመረው የንቅናቄ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ወሳኙ ስራ ተደርጎ እየተከናወነ ነው። ማህበረሰቡ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የአየር ንብረት ፋይናንስ-አፍሪካውያን ገፍተው ያልሄዱበት መንገድ
Feb 18, 2023 1618
/በገዛኸኝ ደገፉ/ የአፍሪካ ቀንድ ከ40 ዓመታት ወዲህ ተከስቶ አያቅም የተባለለትን የድርቅ አደጋ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ ሆነዋል። የድርቁ አደጋ የከፋበት የአፍሪካ ቀንድ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ተሸክመዋል። በተጨማሪም የከተሞች መስፋፋትና የከተሜነት የኑሮ ዘይቤን እያስተናገደች ባለችው አፍሪካ የኃይል እጥረት፣ በቂ የመሰረተ ልማት አውታሮች ዝርጋታ አለመኖር፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት፣ ሥራ አጥነት ብሎም የወንጀሎች መስፋፋት አሕጉሪቱን ክፉኛ እየፈተኗት ይገኛሉ። የገጠር መሬት ምርታማነት መቀነስ ከገጠር ወደ ከተማ ለሚደረገው ፍልሰት አንደኛው ገፊ ምክንያት ሲሆን ለመሬቱ ምርታማነት መቀነስ ሰበብ ተደርጎ በዋናነት የሚጠቀሰው ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት የሚወልዳቸው የውኃ ኃብት መቀነስና ለተከታታይ ዓመታት የሚዘልቁት የድርቅ አደጋዎች መሆናቸው ጉዳዩን ይበልጥ አወሳስቦታል። እንደ አህጉር ከ4 በመቶ ያነሰ የካርቦን ልቀት ያላት አፍሪካ 65 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ መሆን ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። ከዚህ ችግር ሙሉ ለሙሉ መውጣት ባይቻልም ትርጉም ባለው ደረጃ መቀነስ እንዲቻል አህጉሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ኃብትና ወጣት የሰው ኃይል በማስተሳሰር ለውጥ ማምጣት ግድ ይላታል። በአፍሪካ የማይቀረውን የከተሞች መስፋፋትም ሆነ የህዝቦቿን የመልማትና የመለውጥ ፍላጎት ማሟላት ካለባት የአየር ንብረት ፋይናንስን የበለፀጉ ሀገራት ገቢራዊ ሊያደርጉት ይገባል። የአየር ንብረት ፋይናንስ (Climate Finance) የአካባቢ፣ ብሔራዊ ወይም ድንበር ተሻጋሪ ፋይናንስን የሚመለከት ሲሆን ከሕዝብ፣ ከግል እና ከአማራጭ የገንዘብ ምንጮች የተውጣጣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለማስተካከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ስምምነት ነው። የኪዮቶ ፕሮቶኮል እና የፓሪስ ስምምነት ደግሞ ሰፊ የገንዘብ አቅም ካላቸው አገራት አነስተኛ የኃብት አቅም ላላቸው እና ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ አገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ስምምነት ነው። ስምምነቱ “የጋራ ግን ደግሞ ልዩነት ያለው ኃላፊነትና አቅም” በሚለው መርህ መሰረት ያደጉ አገሮች አዳጊ አገራትን ለመርዳት የገንዘብ ምንጮችን እንዲያቀርቡ ይጠይቃል። ፋይናንሱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ወሳኝ ድጋፍ እንደሚሆን ታምኖበታል። ምክንያቱም ልቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ላቅ ያለ የኢንቨስትመንት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ። በተመሳሳይ ከአሉታዊ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎች ጋር ለመላመድ እና ተለዋዋጭ ጫናዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ይጠይቃል። ከጥቂት አሥርት ዓመታት በፊት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበው የምእተ ዓመቱ የልማት ግብ ሰነድም ሆነ በቅርቡ በሚጠናቀቀው ዘላቂ የልማት ግቦች ላይ ለጉዳዩ ከፍ ያለ ትኩረት ቢሰጠውም እስካሁን ግን የፈየደው ነገር የለም። አፍሪካ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችን ለመላመድ ዓመታዊ 41 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የፋይናንስ ክፍተት ይገጥማታል። ይህን ክፍተት ለመሙላት አዲስ አበባ እያስተናገደች ባለችው 36ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ የአየር ንብረት ፋይናንስ ገቢራዊ ማድረግን ቀዳሚ ትኩረታቸው መሆን እንዳለበት የአንድ ዘመቻ (ONE Campaign) አጽንኦት ሰጥቶ ምክረ ሃሳቡን ሰንዝሯል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የአንድ ዘመቻ ዳይሬክተር ዶሪን ኒኒናሃዝዌ የአፍሪካ መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመላመድ ፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥን አስከፊ ተጽዕኖ የመቋቋም አቅም እንዲገነቡ መክረዋል። አፍሪካ ባልፈጠረችው የአየር ንብረት ለውጥ ህዝቦቿ ለከፋ ጥቃት እየተዳረጉ ይገኛሉ። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች የበለጸጉ አገሮች የገቡትን የማላመድ ፋይናንስ ድጋፍ ቃል እንዲፈጽሙ ከማግባባት ባለፈ ማሳሰብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይህ ማለት እኤአ ከ2020 እስከ 2025 በዓመት 100 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመተውን ግብ የማሳካት ተግባር የሚጠይቅ ነው። ከዚህ ባሻገር በቀጣዮቹ ዓመታት በተጨመሩ መዋጮዎች የሚስተዋሉ ጉድለቶችን መፍታት እና በግብጿ ሻርም ኤል ሼክ ከተማ ባስተናገደችው COP-27 ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ለመላመድ በእጥፍ ፋይናንስን የማቅረብ ቁርጠኝነት የማቅረቢያ ዕቅድ ሊነድፉ ይገባል ነው ያሉት። የአፍሪካ አገሮች ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ከሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ጋር ሲታገሉ ቢቆዩም አሁን ላይ “አፍሪካ በአፈፃጸሙ ላይ መጠነኛ መሻሻል አሳይታለች” ብለዋል። እናም በ36ኛው የመሪዎቹ ጉባዔ የተገኙ ስኬቶች እና የጠፉ ዕድሎች እንዲሁም የድርጅቱን ዓላማዎች ለማሳካት በአየር ንብረት ፋይናንስ በጥልቀት መክረው ለተሻለ ስኬት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዋና ዳይሬክተር አንቶኒዮ ቪቶሪኖ በአየር ንብረት ምክንያት የሚፈጠሩ መፈናቀልን ለመግታት የተሻሻሉ የመላመድ እና የተጽዕኖ ቅነሳ ተነሳሽነት ገቢራዊ ለማድረግ በአገራት መካከል ጠንካራ አጋርነትን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ያሰምሩበታል። በተለይ በአፍሪካ ቀንድ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ኑሯቸውን መሰረት ባደረጉ ህዝቦች ላይ አውደ-ተኮር መላመድ እና የመቋቋም አቅም ግንባታ መፍጠር ይገባል። ለዚህ ደግሞ መላመድን የሚደግፉ ፋይናንስ ለማግኘት የሚረዱ መመሪያዎች ይበልጥ የተፍታቱ መሆን ይኖርባቸዋል ሲሉ ቪቶሪኖ ይሞግታሉ። ከ 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በተጓዳኝ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ (High-Level Forum) ላይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በሻርም ኤል ሼክ በተካሄደው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መላመድን፣ መከላከልን እና ዝግጁነትን ለማሻሻል ዓለም አቀፍ ትብብር ማጎልበት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አውስተዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥን አስመልክቶ ያወጣቸው የስምምነት ማዕቀፎች (United Nations Framework Convention on Climate Change (UNFCCC)) በርካታ ዝርዝርና ሚዛናዊ አካሄዶችን የያዙ ናቸው። ያም ሆኖ አተገባበራቸው እዚህ ግባ የማይባል በመሆኑ የሚታሰበውን ያህል ለውጥ ማምጣት ሳይችል ቀርቷል። በዚህም ቦረና ዞንን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የአየር ንብረት መዛባት፣ የሙቀትና የባህር ጠለል መጨመር፣ ጎርፍ፣ ድርቅ እንዲሁም ያልተገመቱ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ዓይነተኛ አማራጭ እንደሆነ ብዙዎቹ ይስማሙበታል። ዳሩ ግን አገራትን፣ አህጉርን፣ ዓለምን እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ግዙፍ ኩባንያዎችን ያስተሳስራል የተባለለት የአየር ንብረት ፋይናንስ በቅጡ ገቢራዊ ማድረግ ባለመቻሉ የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በርካታ ህዝቦች ዳፋውን ለመጋፈጥ ተገደዋል። የአየር ንብረት ፋይናንስን በመተግበር በመስኩ የተጎጂዎችን ቁጥር ሊቀንሱና የዓለምን ሥነ-ምህዳር ከተቻለ ወደ ቀድሞው ሊመልሱ አሊያም አሁን ባለበት አረጋግተው ሊያቆዩ የሚያስችሉ በርካታ አማራጮች ተግባራዊ ሊደረጉ ይገባል። ለአብነትም ለድሃ ሃገራት አርሶ አደሮች የግብርና ምርቶች ተገቢውን ዋጋ በመክፈል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን እንዲቋቋሙ ማድረግ ከአማራጮቹ መካከል አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግዙፎቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሚያስወግዷቸው በካይ ጋዞች ተመጣጣኝ የጤና ሥርዓት በመዘርጋት የታዳጊ ሃገራት ዜጎችን የጤና አገልግሎት ማሻሻል ሌላው አማራጭ ነው። የተፈጥሮ ኃብቶችን የሚጎዱ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ተፈጥሮን በሚንከባከቡ ዘዴዎች መተካት እንዲሁም ብክለትን የሚያስቀሩ የምርት ሂደቶች መለማመድ ጥቂቶቹ የመፍትሄ አማራጮች ተደረገው የሚወሰዱ ናቸው። በፓሪስ ከተደረሰውን የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ቀደም ብሎ በፈረንጆቹ 1994 ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም (Global Environment Facility-GEF) COP-16 ዓለም አቀፍ ጉባዔ በኋላ በ2010 አረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ (Green Climate Fund-GCF) እንዲሁም በ2001 ደግሞ ልዩ የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ (Special Climate Change Fund-SCCF) እና የመላመድ ፈንድ (Adaptation Fund-AF) የተባሉ ማዕቀፎች የተዘጋጁ ቢሆንም ስለጉዳዩ የሚያስረዱ ተከታታይ ስብሰባዎች ከማዘጋጀት በዘለለ ብዙ ርቀት መጓዝ ሳይችሉ ቀርተዋል። በቅርቡ በአለም ባንክ አሰባሳቢነት በኬንያ ናይሮቢ ተዘጋጅቶ በነበረው የአህጉሪቱን መሪዎች ባለሃብቶችንና ምሁራንን ባካተተውና “One Planet Summit” በተሰኘ መሰል ጉባዔ ላይም አፍሪካውያን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚገጥማቸውን ችግሮች ተከላክለው ሁለንተናዊ ዕድገታቸውን እንዲያፋጥኑ ካስፈለገ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምጣኔ ኃብት ፖሊሲ አዘጋጅተው መተግበር እንደሚኖርባቸው መግባባት ላይ የተደረሰ ቢሆንም አሁንም ጥያቄ ያስነሳው አፈጻጸሙ ስለመሆኑ ብዙ ተብሎለታል። ክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ የተባለ ድርጅት ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያመለክተው አፍሪካ እንደ ፈረንጆቹ የጊዜ ቀመር ከ 2020 እስከ 2030 ባሉት አሥር ዓመታት 2 ነጥብ 8 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር አሊያም በየዓመቱ ከ2 መቶ ሃምሳ ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያስፈልጋት ሲሆን አህጉሪቱ ከዘርፉ እያገኘችው ያለው ገንዘብም ከሚያስፈልጋት 12 በመቶውን ወይም 30 ቢሊየን ዶላር ብቻ ስለመሆኑ አስነብቧል። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው ሊሰሩ የሚችሉ በርካታ ተግባራት እንዳሏት የሚያትተው ሪፖርቱ ከአየር ንብረት ፋይናንስ የሚገኘው ገንዘብ በትራንስፖርት፣ በኃይል ልማት፣ በኢንዱስትሪ ብሎም በግብርና፣ በአፈርና በደን ኃብት አጠቃቀም ውጤታማ በሆነ መንገድ ከዋለ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ኃብቶች መንከባከብ ከማስቻሉም ባለፈ ላቅ ያለ ፋይዳ ይኖራዋል ብሏል። ይህ ሲሆን የሥራ ዕድል በመፍጠር የሥራ አጥ ቁጥርን በመቀነስ ለአህጉሪቱ ሰላምና መረጋጋት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖው ያስረዳል። ላለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ገቢራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራን የማስፋፋትና የተጎዱ አካባቢዎችን የማከም ሥራ እንዲሁም አይቀሬ የሆኑትን ከተሜነትና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ታሳቢ ያደረጉ የአየር ንብረት ፖሊሲዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ለአፍሪካ ሃገራት እየፈጠረው ያለው በጎ ተጽዕኖ በግልጽ እየታየ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ጥረት ግን በአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲደገፍ አገራዊና የተቀናጀ አሕጉራዊ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል። ከአጠቃላይ የአፍሪካ አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ግብጽ ብቻ 151 ቢሊየን ዶላር ከአየር ንብረት ንብረት ፋይናንስ ማግኘት እንደሚኖርባቸው የክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ ሪፖርቱ ይገልጻል። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በመጭው የCOP-28 ጉባዔ የራሷንና የአፍሪካን ፍላጎት የሚያስጠብቁ የፋይናንስ ትልሞችን የመንደፍ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባታል፡፡ የ COP-27 ጉባዔ ለአፍሪካ ያስገኘውን ውጤት እና አንድምታ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የመሪዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ እና አስተባባሪ በሆኑት በኬንያው ፕሬዝዳንት ሰብሳቢነት በኅብረቱ የአዲስ አበባ ጉባዔ ላይ በጥልቀት ይገመግማል ተብሎ ይጠበቃል። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ ጥረቷን የሚያጎለብት የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ጠንካራ ተሳትፎ ልታደርግ ይገባል። የአፍሪካ አገራት ገፍተው ረጅም ርቀት ያልሄዱበት የአየር ንብረት ፋይናንስ እና ሌሎች የድጋፍ አማራጮችን በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት በመጠቀም የአየር ንብረት ተጽዕኖን የሚቋቋሙበት ጠንካራ አቅም ሊገነቡ ግድ ይላቸዋል። በእርግጥም አፍሪካውያን መሪዎች በሚያደርጉዋቸው ስብሰባዎች በየማዕዝናቱ በድርቅ ሳቢያ ለምግብ እጦት የተዳረጉ ህዝቦቻቸውን የሚታደጉበት ሁነኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበትን ዘዴ ነድፈው ረጅም ርቀት ሊጓዙ ይገባል። ”
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 1865
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 3460
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 1868
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል።   “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል።   ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 2042
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
በብዛት የታዩ
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 4242
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 4128
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 3759
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 3472
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
በብዛት የታዩ
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 4242
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 4128
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 3759
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 3472
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 3460
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
የአገሪቷ ዓለም አቀፍ ውክልና እንዲጎላ እየተሰራ ነው-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
May 17, 2018 2921
አዲስ አበባ ግንቦት 9/2010 ኢትዮጵያ አሁን በዓለም ካላት የፖለቲካና ዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ እንዲሁም ተሰሚነትና ተደማጭነት ረገድ ያላትን ውክልና ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥቷል። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ መለሰ ዓለም በዚሁ ወቅት እንደተናሩት በሁለተኛው እድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ እንዲከፈቱ ከተያዙ ሚሲዮኖች መካከል በሞሮኮ፣ በአልጄርያና በሩዋንዳ ኤምባሲዎችን፤ እንዲሁም በቱሪክ ኢስታምቡል ቆንስላ ጄነራል መክፈት ተችሏል። በቀጣይ  በርካታ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችን በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በእስያና ኦሺኒያ እንዲሁም በመካክለኛው ምስራቅ አገራት ለመክፈት መታቀዱንም ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል። ይህም ውክልናን ለማስፋት፣ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ለማሳደግ፣ የዜጎችን መብት ለማስከበር፣ የኢንቨስትመንት፣ የቱሪዝም፣ የገጽታ ግንባታ እንዲሁም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ነው የጠቀሱት፡፡ በኢህአዴግ በኩል የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችም ለአገሪቱ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መዳበር የጎላ ሚና እንደሚኖራቸው አቶ መለሰ አብራርተዋል። የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ወገኖች በቅርቡ በአዲስ አበባ የተፈራረሙት የሰላም ስምምነት ማሳለጫ መድረክ እንዲተገበር ኢጋድና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግፊቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በመግለጫው ተጠቁሟል። ለሰላም ስምምነቱ መተግበር በዋና ዋና ተቀናቃኞች በኩል ቁርጠኝነት መኖሩን የገለጹት አቶ መለስ አንዳንድ ቦታዎች የሚታዩ ውጥረቶች ተፈተው ተግባራዊነቱ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 2764
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ
Feb 12, 2023 2695
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 5/2015 በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸናፊ ሆነዋል። ዛሬ ማለዳ በተደረገው ውድድር በወንዶች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1 እስከ 10 እንዲሁም በሴቶች ከ1 እስከ 8 በመውጣት ፍጹም የበላይነትን ይዘዋል። በወንዶች አትሌት አብዲሳ ቶላ 2 ሰዓት ከ5 ደቂቃ ከ42 ሴኮንድ ውድድሩን በመጨረስ አሸንፏል። አትሌት አብዲሳ በአሜሪካ ኦሬጎን በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በተካሄደው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በወንዶች ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ ታናሽ ወንድም ነው። አትሌት ደሬሳ ገለታ እና አትሌት ሃይማኖት አለው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ይዘዋል። በሴቶች አትሌት ደራ ዲዳ 2 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ11 ሴኮንድ በመግባት የውድድሩ አሸናፊ ሆናለች። አትሌት ደራ የአትሌት ታምራት ቶላ ባለቤት ነች።አትሌት ሩቲ አጋ እና አትሌት ስራነሽ ይርጋ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል። በሁለቱም ጾታዎች ያሸነፉት አትሌቶች በተመሳሳይ የ80 ሺህ ዶላር ሽልማት ያገኛሉ። በተያያዘ ዜና ዛሬ ማለዳ በተካሄደው የሆንግ ኮንግ ማራቶን በሴቶች አትሌት ፋንቱ ኢቲቻ 2 ሰዓት ከ27 ደቂቃ ከ51 ሴኮንድ በመግባት አሸንፋለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ አትሌት ስንቄ ደሴ ሁለተኛ ወጥታለች።በወንዶች ኬንያዊው አትሌት ፊልሞን ኪፕቶ ኪፕቹምባ አሸንፏል። ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች ልመንህ ጌታቸው እና ሰንበታ ገዛ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።
መጣጥፍ
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 2634
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ)
Jan 25, 2023 2485
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ) አየለ ያረጋል (ኢዜአ) መዳረሻዬ ሽሬ እንዳስላሴ ነው። ለዘገባ ሥራ ከባህርዳር- ጎንደር- ደባርቅ- ሸሬ መንገድ ከሚዲያ ባልደረቦች ጋር እየተጓዝኩ ነው። የጥምቀት ሙሽራዋ ጎንደር እየተኳኳለች ነበር። ደባርቅ ከመድረሴ በፊት ዳባት ትገኛለች-የደጃች አያሌው ብሩ ቁርቁር ከተማ። ደጃች አያሌው ትውልዳቸው በጌምድር ጋይንት ቢሆንም ግዛታቸውና ኑሯቸው ዳባት ነበር። ሞገደኛው ደጃዝማች አያሌው ብሩ በጎንደር ማኅበረሰብ ዘንድ ዝናቸው የናኘ ነው። ደጃዝማች አያሌው በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ (ከልጅ ኢያሱ እስከ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ-መንግሥት) ታሪካዊ ክንውኖች ጉልህ ተሳትፎ አላቸው። አንዷን ብቻ ልምዘዝ። ራስ ተፈሪ ‘ንጉሠ-ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ’ ደጃች አያሌው የቅርብ ዘመዳቸውን ራስ ጉግሳ ወሌ ብጡልን (የንግሥት ዘውዲቱን ባለቤት) ወግተው የጎንደር ግዛት ‘ራስ’ ተብለው ለመሾም ቃል ቢገባላቸውም፤ ተልዕኳቸውን ተወጥተው ቃሉ ባለመፈጸሙ ደጃዝማቹ ከአጼው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። በዚህም:- "አያሌው ሞኙ፣ ሰው አማኙ ሰው አማኙ፣ የአያል ጠመንጃ፣ ስሟን እንጃ ስሟን እንጃ…” በማለት የጎንደር አዝማሪ አዚሟል። ዛሬም ይህ ግጥም የብዙ ባህላዊ ዘፈኖች አዝማች ነው። ደጃች አያሌው ብሩ ደፋር ናቸው ይባላል። ከአጼ ኃይለሥላሴ ጋር ቢቀያየሙም በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ሲመጣ ቅድሚያ ለአገሬ ብለዋል። ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘው የዶክተር ሀራልድ ናይስተሮም (ትርጉም ገበየሁ ተፈሪ እና ደሳለኝ አለሙ) መጽሐፍ እንደተጠቀሰው ደጃች አያሌው “ንጉሡ እንደኛ ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ ግን የሁላችንም ናት" ብለው ጦራቸውን መርተው በሽሬ ግንባር ዘምተዋል። ጉዟችን ቀጥሏል። ደባትን እያለፍን ነው። ‘እንኳን ደህና መጡ፤ ወደ ጭና ታሪካዊቷ ሥፍራ’ የምትለዋን ታፔላን በስተግራ እያየን ወደ ደባርቅ ገሰገስን። የሰሜን ተራሮች የብርድ ወጨፎ ያረሰረሳትን ደባርቅን ከማለፋችን ሊማሊሞ ጠመዝማዛ ቁልቁለት ተቀበለን። አስፈሪ የሊማሊሞ መልክዓ ምድር የደጋው ሰሜን ውርጭ እና የተከዜ በርሃ ኬላ ነው። ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድህን “የሰማይ የምድሩ ኬላ፣ የየብስ የጠፈሩ ዋልታ አይበገር የዐለት ጣራ፣ አይመክተው መከታ ሊማ-ሊሞ አድማስ ሰበሩ፣ በጎማ ፈለግ ይፈታ? በትሬንታ እግር ይረታ?…” ብሎ የመኪና መንገድ ተገንብቶበት በማየቱ ግርምቱን የተቀኘለትም ለዚህ ይመስላል። ከሊማሊሞ ቁልቁለት በኋላ አዲ-አርቃይ፣ ዛሪማ፣ ማይፀብሪ እና ሌሎች የጠለምት ወረዳ ከተማዎችን አልፈን፤ የዋልድባ ረባዳማ አካባቢዎችን ተሻግረን ተከዜ ወንዝ ደረስን። የዚህን መንገድ እና ተከዜ ወንዝን ሳስብ የሀዲስ ዓለማየሁ ትዝታ አስተከዘኝ። የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ጦር የወገንን ጦር ፊት ለፊት መቋቋም ሲሳነው በሰው ልጆች ላይ ተደርጎ የማያውቅ መርዝ በጅምላ የፈጀበት አሳዛኝ ታሪክ ነበር። በተከዜ ወንዝ ውሃን በመመረዝ የወገን ጦር ያለቀበት ሥፍራ ነው። የተከዜ ሸለቆ በኢትዮጵያዊያን ደምና አጥንት ዋጋ የተከፈለበት ነው። ሀዲስ ዓለማየሁ በአንድ ዕለት የተመለከቱትን እንዲህ ጽፈውታል። “የተከዜ ውሀ እመሻገሪያው ላይ ሰፊና ፀጥ ያለ ነው። ታዲያ ያ ሰፊ ውሀ፤ ገና ከሩቅ ሲያዩት ቀይ ቀለም በከባዱ የተበጠበጠ ይመስላል። “ምን ነገር ነው፤ ምን ጉድ ነው?” እየተባባልን ቀረብ ስንል መሻገሪያው በቁሙም በወርዱም ከዳር እስከ ዳር ሬሳ ሞልቶበት የዚያ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው። የሰው ሬሳ፣ የፈረስ እና የበቅሎ ሬሳ፣ ያህያ ሬሳ፣ ያውሬ ሬሳ፥ ሬሳ ብቻ! እግር ከራስ ራስ ከእግር እየተመሰቃቀለ እየተደራረበ ሞልቶበት፥ የዚያ ሁሉ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው”። ይሉናል። ቀጥለውም “በእውነቱ እንዲህ ያለውን መሳሪያ ምንም ጠላት ቢሆን በሰው ላይ ለማዋል የሚጨክን ሰው፥ ሰብዓዊ ስሜት የሌለው፣ አለት ድንጋይ የተፈጠረበት መሆን አለበት፤ እንዲህ ያለውን መሳሪያ በሰው ላይ ማዋል ሰብዓዊ ህሊና ሊሸከመው የማይችል እጅግ ከባድ መሆኑን ዓለም ሁሉ ያወቀውና ያወገዘው በመሆኑ የኢጣሊያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ከማድረጉ በቀር “ሌላ መንግሥት በሌላ አገር ላይ አደረገ’ ሲባል ተሰምቶ የሚያውቅ አይመስለኝም” ብለዋል። ከተከዜ ባህር ማዶ ጉዞዬ ያገኘኋት ሌላዋ ታሪካዊ ሥፍራ እንዳባጉና ናት። እንዳባጉና የወገን ጦር ትልቅ ገድል የፈጸመበት ነው። ጀግኖች አባቶቻችን የጠላት ታንክ ሳያስፈራቸው የጠላት ጅምላ ጨራሽ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ተቋቁመው ጠላትን ድባቅ የመቱበት፤ ወደ አክሱም እንዲያፈገፍግ ያደረጉበት ሥፍራ ነው። “የጠላት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በጦር ሜዳው ትንንሽ ቦምቦች አውቶማቲክ ጠመንጃ ይተኩስ ነበር። አቢሲኒያኖች ደግሞ ከጠላት ጋር ግብግብ ገጥመው ጉዳይም አልሰጡትም ነበር…” ይላል ዶክተር ሀራልድ ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘ መጽሐፉ። ይህ አካባቢ በሀገር ፍቅር የነደዱ ኢትዮጵያዊያን ደም ያፈሰሱበት፣ አጥንት የከሰከሱበት፤ ለኢትዮጵያ መስዕዋትነት የከፈሉበት ነው። ይህ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ቀጣና ነው። ቀኑ ተገባዷል። ጉዟችን እንደቀጠለ ነው። እኔም የማሽላ ማሳዎችን ግራ ቀኝ እየተመለከትኩ ለዕለቱ መዳረሻችን ወደሆነችው ሽሬ ከተማ ገባን። ሽሬ በትግርኛ ‘ሽረ’ ሲሉት ይደመጣሉ። በእርግጥ ሽሬን ለመጀመሪያ ጊዜ መርገጤ ነው። ዕለቱም ጥር ሥላሴ ነው። ሽሬ በጥር ሥላሴ ትደምቃለች፤ ሙሉ ስሟም ሽረ እንዳስላሴ ነው። የሽሬ ሥላሴ ጠበል ሽሬ ደርሰን ማረፊያችንን ያዝን። ጊዜው በጣም አልመሸምና ከተማዋን በቀላሉ መቃኘት ይቻላል። ሽሬ ሰፊና ደማቅ የዞን ከተማ ናት። ከመካከላችን የአንደኛው ባለሙያ ቤተሰቦች ሽሬ ነበሩና አስጠሩን። ለሥላሴ ጠበል ግብዣ። ባል እና ሚስቱ ከልክ በላይ መስተንግዶ አደረጉልን። ‘ጠብ እርግፍ አድርገው አስተናገዱን’ ማለት ይቀላል። እንግዳ መቀበል ነባር ኢትዮጵያዊ እሴታችን ቢሆንም ጦርነት ውስጥ ለቆየ አካባቢ የተለየ መልክ ነበረው። እንግዳ አቀባበላቸው በእርግጥም የመሃል አገር ሰው የናፈቃቸው ይመስላል። የተትረፈረፈ እህልና ውሃ አቅርበው በ’ብሉልን፤ ጠጡልን’ ተማጽኗቸው የተነፋፈቀ ቤተ-ዘመድ ግብዣ አስመሰሉት። የሥላሴው ጠበል የሸሬ ጠላ ቀረበ። የሸሬ ጠላ ሳስታውስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ታወሱኝ። የወቅቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምሀሩ ፕሮፌሰር ሽብሩ በዘመነ ደርግ በዕድገት በሕብረት ዘመቻ ተማሪዎቻቸውን ይዘው ሽሬ ዘምተው ነበር። በወቅቱ ታዲያ የሸሬ ጠላ ፍቅር ይዟቸው በየጊዜው ሲኮመኩሙ የተመለከቱ ሰዎች ‘ፕሮፌሰሩ ከጠፉ የሚገኙት ጠላ ቤት ነው’ ሲባሉ እንደነበር ‘ከጉሬ ማርያም እስከ አዲስ አበባ’ በተሰኘው ግለ ታሪካቸው አስፍረዋል። ከግብዣ መልስ ከማረፊያ ሆቴል ላይ ሆኜ ከተማዋን ስቃኛት ከጦርነት ድባቴ የተላቀቀች ይመስላል። የአመሻሽ ሕዝቡ እንቅስቃሴም ሆነ እስከ ሌሊቱ አጋማሽ የሚሰሙ የመዝናኛ ቤቶች ሙዚቃዎች የከተማዋን አሁናዊ መልክ የገለጠልኝ ነበር። ንጋት ላይ በቁርስና ቡና ሰዓታት ከሰዎች ጋር መስተጋብሬ ጀመረ። በጦርነት አዙሪት የከረመችው ሽሬና አካባቢው ኑሮ እጅጉን የከበደ ነበር። መልከ-ብዙ ማህበራዊ ቀውሶች አስተናግደዋል። አሁናዊ ምላሻቸው “ተመስገን፤ ያ ሁሉ አለፈ” የሚል ነው። ገበያው ተረጋግቷል፤ ማህበራዊ ኑሮ ተመልሷል። ድህረ-ሰላም ስምምነት ለሽሬ ነዋሪዎች ሁለንተናዊ እፎይታን አንብሯል። ከቀናት በኋላ በአክሱም የታዘብኩትም እንዲህ ነው። ኑሮን ያቀለለው የተቋማት አገልግሎት ጅማሮ በመጀመሪያ ዘገባ ስራዬ መሰረተ ልማትን አገልግሎት ቃኘሁ። ባንክ፣ ቴሌ፣ ሆስፒታል… መሰሎቹን። ተጠቃሚዎችንም፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ስራ ሃላፊዎችንም አነጋገርሁ። ከሰላም ስምምነቱ ማግስት ጀመሮ ተቋማቱ ወደስራ መመለሳቸው ከሁለንተናዊ ችግር እንደታደጋቸው ያነሳሉ። በትራንስፖርት እየተንቀሳቀሱ፣ በኤሌክተሪክ ስራዎቻቸውን እየከወኑ ነው። ለሁለት ዓመታት የተቋረጠው አገልግሎት አቅርቦት እና የአገልግሎት ፈላጊዎች ፍላጎት ግን አሁንም ሙሉ በሙሉ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ የተጠቃሚዎችም፤ የአገልግሎት ሰጭዎችም ሀሳብ ነው። በሽሬ ስሁል ሆስፒታል የተመለከትኳቸው፤ ያነጋገርኳቸው፤ ከታዳጊዎች እስከ አዛውንት ዕድሜ ያሉ ህሙማን የሰላም አየር ማግኘታቸው የሕይወታቸው ዑደት እንዲቀጥል አድርጓል። ድንገተኛም ሆነ ነባር ህመም ያለባቸው ሰዎች በነጻ እየታከሙ ነው ያገኘኋቸው። ሰላም ከሌለ መታከም ቀርቶ በቅጡ ማስታመም፤ በወጉ መቀበርም እንደማይቻል ገልጸውልናል። የጤና፣ የባንክና የቴሌኮም አገልግሎት የግብዓት ክፍተቶች የማሟላት ሰራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም በፌዴራል ደረጃ በየተቋማቱ የተመደቡ አስተባባሪዎች አረጋግጠውልኛል። የጸጥታ አካሉና የህብረተሰቡ ትብብርም የሚያስቀና እንደሆነ ግለሰቦችም፤ የጸጥታ አካላትም ነግረውኛል። አክሱም ጺዮን ማርያም፣ ሽሬ ስላሴ ንግስ፣ የጥምቀት በዓላት ከሶስት ዓመታት በኋላ በአደባባይ ታቦት ወጥቶ ተከብሯል። የፌዴራል ፖሊስ ተወካዮችም ይህንኑ ነው ያረጋገጡልኝ። የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከከተማ ነዋሪዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት ቤተሰባዊ የሆኑ ይመስላል። እንቅስቃሴያቸውም የሰላማዊ ቀጠና መልክ ያለው ነው፤ ዩኒፎርም ከመልበሳቸው በስተቀር ጀሌያቸውን ይንቀሳቀሳሉ። ይህ ደግሞ መተማመን ከመፍጠር ባለፈ ጦርነት ውስጥ ለቆየ ማህበረሰብ ከስነ ልቦና ጫና እንዲላቀቅ አይነተኛ ሚና እንደላው ይሰማኛል። ኢ-መደበኛ የሽሬና አክሱም ወጎች ያረፍኩበት ሆቴል ባለቤት ‘አደይ’ ተግባቢ ናቸው። ደግ እናት ይመስላሉ። ከገባን ጀምሮ ‘ጠላ ተጎንጩ፤ ቡና ጠጡ’ ጭንቃቸው ነው። ሁለት ቀን ቡና አስፈልተውልናል፤ ጠላ አቅርበው ዘክረውናል። ይህ ሁሉ ሲሆንም ለከተማው እንግዳ መሆናችንን እንጂ ስለሙያችንም ሆነ ስለሌላ ማንነታችን አያውቁም ነበር። ብዙ መጨዋወትና ውሎ አዳር በኋላ ነው ጋዜጠኛ ስለመሆናችን ያወቁት። አደይ ተጨዋች ናቸው። አማርኛ ያዝ ቢያደርጋቸውም ጨዋታቸው ‘ኩርሽም’ ነው- ተሰምቶ የማይሰለች። በአጋጣሚ ‘ሰለክላካ’ ስለምትባለዋ ታሪካዊ ሥፍራ ጠይቄያቸው እያወጋን ነበር። ‘እንደእናንተ ወጣቶች ሳለን ‘ሰለክላካን ያላዬ ሸዋን ያመሰግናል’ ይባል ነበር። ታዲያ አንድ የሸዋ ሰው መጣና ሰለክላካን አየና ‘በቃ ይቺ ናት’ ሰለክላካ’ ብሎ ተገረመ” ብለው አሳቁን። (የፍቅር እስከ መቃብር መሪ ገጸ-ባህሪው ‘በዛብህ’ ወደ ዲማ ጊዮርጊስ ሄዶ ‘የዲማ መልኳ እና ዝናዋ’ ተጣርሶበት እንደተገረመበት ቅጽበት መሆኑ ነው)። አደይ የተጀመረው ሰላም ፍጹም ምሉዕ ሆኖ ወደ ቀደመ ኢትዮጵያዊ መልካችን የምንመለስበት ጊዜ እንዲመጣ ይሻሉ። ከጦር-ነት ወደ ሰላም-ነት! ቆንጂዬዋ ፊዮሪ የኮሌጅ ተማሪ ነበረች። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጀምሮ በኋላም በጦርነት ሳቢያ ትምህርቷን ካቆመች ሦስት ዓመታት ሆኗታል። ጦርነቱ ከቆመ በኋላ የጀበና ቡና ጀምራለች። ደንበኞቿ ሰብሰብ ብለን እንቀመጣለን። ፊዮሪ ከስኒ ማቅረቢያዋ ላይ አነስተኛ ጀበናዋን፤ የሚያማምሩ ስኒዎቿን እና መዓዛው ከሚያውድ የዕጣን ማጨሻዋ ጋር ሰድራ ይዛ ትቀርባለች። ከመካከላችን ካለው ጠረጴዛ ላይ ታስቀምጥና እርሷም ወንበር ይዛ ከመካከላችን ትቀመጣለች። ቡናው እስኪሰክን ጨዋታዋን ታስኮመኩመናለች። ቡናው ከሰከነ በኋላ ቡናዋን ቀድታ ለእያንዳንዳችን በእጃችን እያነሳች ትሰጣለች። በሽሬ ቡና የሚቀርበው በዚህ መልክ ነው። ለፊዮሪ እና መሰሎቿ ጦርነቱ ክፉ ጠባሳ መጣሉ፤ ተስፋቸው ላይ መጥፎ አሻራ ማስቀመጡን ታነሳለች። አሁን ግን ብሩህ ተስፋ ሰንቃለች። ስለነገዋም “ሰላሙ ይዝለቅልን፤ ትምህርቴን ለመቀጠል እመኛለሁ” ትላለች። አክሱም ከሽሬ በስተሰሜን 60 ኪሎ ሜትር ይርቃል። ከሽሬ አክሱም ስንንቀሳቀስ ከጥምቀት ዕለት በስተቀር ገበሬው የግብርና ሥራዎቹን እየከወነ ነበር። አርሶ አደሩ ያርሳል፤ መስኖውን ያለማል። የተዘራውን ውሃ ያጠጣል። የበቀለ ቡቃያውን ይኮተኩታል። ከጦርነት ወደ ልማት መዞሩን ዐይኔ ታዝቧል። በጥምቀት ዋዜማ፤ የከተራ በዓል ዕለት ሁለት ጎራማይሌ የረፋድ ትዕይንቶችን ላንሳ። ከአክሱም ከተማ ወደ አድዋ እና ሽሬ መገንጠያ አካባቢ ሰፊ የቀንድ ከብት ገበያ ነበር። እውነተኛ የዓመት በዓል ገበያ መልክ ያለው ትዕይንት ነበር። በተለይም የፍየል ዋጋ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተገበያዩ እንደነበር ሰምቻለሁ። ታሪካዊቷን አክሱም ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ የረገጥኳት/የተሳለምኳት ከአራት ዓመት በፊት በ2011 ዓ.ም ይመስለኛል። ከገበያው ቀጥሎ በታቦተ-ጽዮን መገኛዋ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ደጅ፣ በጥንታዊያኑ የአክሱም ሐውልት መገኛ አደባባይ ነበር። ከጽዮን በስተምዕራብ በአርባቱ እንሰሳ በኩል፤ በቅዱስ ያሬድ ዋርካ… አድርጌ በጽዮን ዋናው በር ደረስኩ። ማራኪ የአክሱም የኮብልስቶን መንገዶች ኦና ናቸው። የወትሮው ግርግር ናፍቋቸዋል። ከጽዮን ቅጥር ግቢ በዋናው በር በስተውጭ አነስተኛ እና ብቸኛ ዋንዛ በኮብልስቶን መሃል ነበረች። ዛሬም ለምልማ አለች። በዚህ አካባቢ ድሮ የነጭ ጎብኚ ጋጋታ፣ የጽዮን ደጅ ጠኚ ምዕመን… የተጨናነቀ ነበር። እንደ ድሮው የፎቶ አንሺ ግርግር፣ የአክሱም መስቀል ቀርጸው የሚሸጡ ወጣቶች ጫጫታ የለም። ይልቁንም እርጥባን የሚሹ አቅመ ደካሞችና ህፃናት ነበሩ። ጦርነት የሥፍራዋን መልክ አጠይሞታል። ያም ሆኖ ከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ሙሉ በኩሉሄ ባይባልም ወደነበረበት እየተመለሰ ነው። የግልም ሆነ የመንግሥት ባንኰች ሥራ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከአክሱም ሐውልት ወደ ሌላ ሰፈር አቀናሁ። ትርሐስ ገና ታዳጊ ልጅ ነች። ጠይም፤ ስርጉድ፣ ሳቂታና ተረበኛ አይነት ልጅ ነች። እንደ ሽሬዋ ፊዮሪ መንገድ ዳር የጀበና ቡና እየሰራች ነው። ከሩቅ የመጣን እንግዶች መሆናችንን ስታውቅ፤ ደስታዋ ከገጿ ይነበብ ነበር። ያለፉ ጊዜያትን ሰቆቃ አጫወተችን። ስለቀጣይ ዕጣ ፈንታዋ እና ዕቅዷ ስታወራ ትቆይና “የሰው ልጅ ግን በጣም ከሃዲ ነው። ከወራት በፊትኮ ስለቢዝነስ አላስብም ነበር። መቼ እሞታለሁ እንጂ” ብላ ራሷን ትወቅሳለች። ወደ ሰማይ አንጋጣ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች። ጦርነት ተራውንም ሕዝብ ለመልከ-ብዙ ቀውስ ዳርጎት እንደቆየ ታነሳለች። ዛሬ ሁሉ አልፎ ሰላም መውረዱ ለመጨዋወት መብቃቷ ለእርሷ ትልቅ ብሥራት ነው። ይህ ለትርሐስ ብቻ ሳይሆን ለመላው አክሱማዊያን መሆኑ እሙን ነው። አክሱም ከተማ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ከዋለችበት ጊዜ ጀምሮ በከተማዋ በሻለቃ አዛዥነት የተሰማራ የፌደራል ፖሊስ አባልም ያጋጠመውን አሳዛኝ ገጠመኞች አጫውቶኛል። ጦርነቱ ቢራዘም ኖሮ በተራው ሕዝብ ላይ ምን ያህል የከፋ ጉዳት ይደርስ እንደነበር በአሳዛኝ ሁኔታ ገልጾልኛል። አክሱሞች ያን ሁሉ አልፈው ሰላም አየር ነፍሶ፣ ከስጋት ቆፈን ተላቀው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ተመልሰዋል። የዛሬ ሳምንት ሰርክ(11 ሰዓት) ላይ አክሱም የከተራ በዓል በድምቀት አክብራለች። ታቦተ-ጽዮን ወደ ባህረ- ጥምቀቱ ስትወርድ፤ ወግና ሥርዓቱ ተጠብቆ፣ ሕዝቡ በሀበሻ ነጫጭ አልባሳት፣ ካህናት በልብሰ ተክህኖ ደምቀው … እየተከወነ ነበር። አንዲት እናት ለአማርኛ ተናጋሪ በቀረበ አነጋገር እያለቀሱ ታቦት እየሸኙ ነው። ትኩር ብዬ ሳያቸውም ዕንባቸው ዱብ ዱብ ይላል። “ከዚያ ሁሉ መከራ አልፎ ለዚህ በቃን፤ ተመስገን” እያሉ እልልታውን ያቀልጡታል። በደስታ እያነቡ ነበር። ይህ ስሜት የብዙኃኑ አክሱማዊያን እናቶች እንደሆነ መገመት ቀላል ነው። አክሱም በኮቪድ እና በኋላም በጦርነቱ ምክንያት ባህረ-ምቀት ታቦት ወጥቶ ሲከበር ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ከወትሮው በተለየ ድምቀትና ውበት በሰላምና በደስታ፤ በአደባባይ እልልታና ሆታ በማክበራቸው ልዩ ስሜት ፈጥሮባቸዋልና! እናም በአክሱም የከተራ ሆነ የበዓለ-ጥምቀት ክብረ-በዓላት በሰላም ስምምነቱ ማግስት በድምቀት ተከውኖ አለፈ። የሃይማኖት አባቶቹም ሆኑ ምዕመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅም የዘንድሮው ክብረ-በዓል ካለፉት ዓመታት ነባራዊ ሁኔታ ጋር እያነጻጸሩ፤ ትልቅ ብሥራትና መልክ እንዳለው ገልጸዋል። ሰላም እንዲጸና፤ ነባር ኢትዮጵያዊ አንድነትና መተባበር እንዲመለስ ጽኑ መሻታቸውን ነግረውናል። በበጎ ቀን የማውቃትን አክሱም፤ ከረዥም ጊዜ በኋላ አሁናዊ መልኳን ታዝቤ፤ የነገ ትዝታ ሰንቄ ተመለስኩ!! ሰላም ለኢትዮጵያ!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም