ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ ባንክ ጋር የአምስት ዓመት የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ
Nov 20, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ ባንክ ጋር የአምስት ዓመት የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 25ኛ ዓመት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ አትሌቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በኃይሌ ግራንድ ሆቴል ተከብሯል። ከዚህም ባሻገር የአሜሪካ ባንክ (Bank of America) ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር እ.ኤ.አ ከ2026 ጀምሮ ለአምስት ዓመት የሚያቆየውን የአጋርነት ስምምነት ተፈራርሟል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መስራች አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በዚህ ወቅት፤ ስምምነቱ ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር ሳይሆን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የተደረገ መሆኑን ገልጿል። የአሜሪካ ባንክ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ለማስፋት ወደ ኢትዮጵያ ስለመጣ ምስጋና አቅርቧል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 25ኛ ዓመት ከአሜሪካ ባንክ ጋር አጋርነት የተፈራረምንበት ትልቁ የደስታዬ ቀን ነው ብሏል። ስምምነቱ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያን አቅም ለማሳደግ ትልቅ የመሰረት ድንጋይ መሆኑንም ገልጿል። የአሜሪካ ባንክ ዓለም አቀፍ የገበያ ትብብር ኃላፊ ብራድ ሮዝ በበኩላቸው፤ የዓለም አሻራ ከሆነው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር ለአምስት ዓመታት ስለምንሰራ ኩራት ይሰማናል ብለዋል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አንድነትን የሚፈጥር፣ የኢኮኖሚ መነቃቃትን የሚያሳልጥ መሆኑንም ገልጸዋል።
የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የክብርና የኢኮኖሚ ነፃነት ጉዳይ ነው
Nov 20, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የአህጉሪቷ የክብርና የኢኮኖሚ ነፃነት ጉዳይ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ አዘጋጅነት የአፍሪካ ሀገራትን የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥን ዓላማ ያደረገ ዓለም አቀፍ ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፤ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የአህጉሪቷ የክብርና የኢኮኖሚ ነፃነት ጉዳይ ነው ብለዋል። የአህጉሪቷን ዜጎች የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረትም ከተረጂነት በመላቀቅ የማይበገር የግብርና ሥርዓት የመገንባት አካል መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያም በዘመናዊ የግብርና ሥርዓት ምርታማነትን በማሳደግ ቀጣይነት ያለው የምርት ተወዳዳሪነት ዕድገት እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በሜካናይዜሽን የእርሻ ሥርዓትን በመደበኛና መስኖ ግብርና ምርታማነት ግልጽ ስትራቴጂክ ዕቅድ ነድፋ እየሰራችበት መሆኗንም አብራርተዋል። በስንዴ ምርታማነት የተመዘገበው ዕድገትም ከጥገኝነት በመላቀቅ ለውጭ ገበያ ማቅረብ ያስቻለ ተጨባጭ ስኬት ማስመዝገብ እየተቻለ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በኢትዮ-ሩሲያ መካከልም በትብብር ላይ የተመሰረተ ረጅም ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ሥርዓት በሚያሻሽሉ ዘላቂና ስትራቴጂክ የልማትና ኢንቨስትመንት የትብብር መስኮች በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን አስረድተዋል። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተርኪሂን፤ ሩሲያ የአፍሪካን ልማትና ዕድገት በመደገፍ የአህጉሪቷ ጠንካራ አጋር ነች ብለዋል። በቀጣይም የአፍሪካን የግብርና ሥርዓት ለማዘመን በሚደረገው ጥረት ለአህጉሪቷ የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ያሉት አምባሳደሩ፤ ለዚህም ከራሷ አልፎ ለውጭ ገበያ ጭምር ለመትረፍ በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኗ የሚደነቅ ነው ብለዋል።
ቴሌብር የፋይናንስ ተደራሽነት እና አካታችነትን ለማስፋት አስችሏል
Nov 20, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ቴሌብር ተጠቃሚዎች በቀላሉ የፋይናንስ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ ተደራሽነትና አካታችነትን ለማስፋት ማስቻሉን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ኢትዮ ቴሌኮም ከአዋሽ ባንክ ጋር በመተባበር "ጥላ" የተሰኘ አዲስ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት በቴሌብር አማካኝነት አስጀምሯል። ይህ ትብብር የሀገሪቱን የፋይናንስ አካታችነት ለማስፋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ኢትዮ ቴሌኮም የሀገሪቷን ዲጂታል ኢትዮጵያ ራዕይ እውን ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል። ቴሌብርን በመጠቀም በቀላሉ የፋይናንስ አገልግሎት ማግኘት መቻሉን አመልክተው፤ ይህም ለተጠቃሚዎቹ ምቹ፣ ፈጣን እና ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ተደራሽነት እንዲሰፋ ማድረጉን አንስተዋል። ቴሌብር የቴክኖሎጂ አቅምን ከባንክ ተቋማት የፋይናንስ ልምድ ጋር የተጣመረበት መሆኑን ጠቅሰው፤ የፋይናንስ አገልግሎትን ወደ ህብረተሰቡ በስፋት እንዲደርስ እያደረገ እንደሚገኝም አብራርተዋል። ከአዋሽ ባንክ ጋር የተደረገው አጋርነትም ሁለቱ ተቋማት የየራሳቸውን ጥንካሬ ለሀገራዊ ልማት ለማዋጣት እንደሚያስችላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ አስረድተዋል። "ጥላ" ዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ምቹ፣ ፈጣን እና ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ አገልግሎት የበለጠ ለማስፋት እንደሚረዳ ተናግረዋል። የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፀሀይ ሽፈራው በበኩላቸው፤ "ጥላ" የባንኩን የዲጂታል ለውጥ ለማፋጠን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በቴሌብር በኩል የሚቀርቡት እንደ ማይክሮ ብድር (Micro Credit)፣ የሞባይል ቁጠባ (Mobile Saving) አገልግሎቶች ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው እና አነስተኛ ንግድ ለሚሰሩ ትልቅ ዕድል ይፈጥራሉ ብለዋል። በቀጣይም ሁለቱ ተቋማት ተጨማሪ አዳዲስ እና ፈጠራ ያላቸው የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማጠናከር እንደሚሰሩ ጠቁመዋል። "ጥላ" የፋይናንስ ዲጂታል አገልግሎት የቁጠባ፣ የግለሰብ ብድር፣ ለአነሰተኛ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ብድር እና የዲቫይስ ፋይናንስ አገልግሎቶች በአንድ ጥላ ስር ለመስጠት የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
የኩላሊት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Nov 20, 2025 52
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የኩላሊት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የጤና ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ስር የሰደደ ኩላሊት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል መርሃ ግብር አስጀምሯል። ሚኒስቴሩ መርሃ ግብሩን ያስጀመረው ከፖፕሌሽን ሰርቪስ ኢንተርናሽናል (ፒ ኤስ አይ ) እና አስትራዜኒካ ከተሰኙ መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ሲሆን ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት እንደሚተገበር ተገልጿል። መርሃ ግብሩ በጤና ጣቢያዎችና መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ስር ለሰደደ ኩላሊት በሽታ አጋላጭ የሆኑ ግፊት እና ስኳር በሽታዎችን ምርመራ በማድረግ መለየት እና ህክምና የሚሰጥበት ሥርዓት ያካተተ ነው። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ እንዳሉት፤በኢትዮጵያ ስር የሰደደ ኩላሊት ታማሚዎች ቁጥር ከ6 በመቶ በላይ ነው። ለዚህ ደግሞ ዋነኛ መንስኤ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል የደም ግፊትና ስኳር በሽታ እንደሚገኙበት ጠቁመው መሰል ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ ለመከላከል እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም ሚኒስቴሩ የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ አውጥቶ እየተገበረ መሆኑን ጠቁመው ዜጎች ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች አጋላጭ ከሆኑ የአኗኗር ዘይቤዎች ራሳቸውን እንዲጠበቁ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። አካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ስብ የበዛበትና ጤናማ ያልሆነ አመጋገብ አጋላጭ መሆኑን ጠቅሰው ህብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ ጨብጦ ራሱን እንዲጠብቅ እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። ሚኒስቴሩ ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን ይፋ ያደረገው መርሃ ግብር በጤና ጣቢያዎችና መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች የግፊትና ስኳር ምርመራ እና ልየታ የሚያደርጉ የጤና ባለሙያዎች አቅም መገንባት፣ለህክምና የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በሟማላት አገራዊ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል። ፖፕሌሽን ሰርቪስ ኢንተርናሽናል (ፒ ኤስ አይ ) የኢትዮጵያ ቢሮ ተጠባባቂ ተወካይ ሩት ወልደትንሳኤ በበኩላቸው፤ ስር የሰደደ የኩላሊት በሽታን በኢትዮጵያ ያለበትን ደረጃ ለማወቅ የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት መደረጉን ተናግረዋል። ጥናቱን መሰረት በማድረግም በቀጣይ የሚወሰዱ እርምጃዎች አቅጣጫዎች መቀመጡን አስረድተዋል። ስር ለሰደደ ኩላሊት በሽታ አጋላጭ የሆኑት ግፊትና ስኳር በሽታዎች ምርመራ የሚያደርጉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ሥልጠና እንደሚሰጡም አመልክተዋል። የኩላሊት ጤንነትን ለመጠበቅ የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ህብረተሰቡ የኩላሊት ጤና የሚያስጠብቅበት መንገዶች ላይ በዘመቻ መልክ ግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባራት እንደሚከናወኑም አስረድተዋል። ከሳሃራ በታች ያሉ አፍሪካ አገራት የአስትራዜኒካ ቢሮ ዳይሬክተር አሚት ባክሪ በበኩላቸው፤ አስትራ ዜኒካ "ሄልዚ ሀርት አፍሪካ" በተሰኘ መርሃ ግብር በኩል በአፍሪካ 77 ሚሊዮን አፍሪካዊያን የደም ግፊት ተጋላጭነት ምርመራ ማካሄዱን ተናግረዋል። ለ11 ሺህ 890 የጤና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠቱን ገልጸዋል። አስትራዜኒካ ሰፊ ልምድ አለው ያሉት ዳይሬክተሩ ስር የሰደደ የኩላሊት በሽታ አስቀድሞ መከላከል ላይ ከኢትዮጵያ ጋር በአጋርነት በመስራታችን ደስተኞች ነን ብለዋል።
እውቅናው ለበለጠ ድል የሚያነሳሳ ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Nov 20, 2025 79
አዲስ አበባ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-የዓለም አትሌቲክስ ለሻምበል አትሌት አበበ ቢቂላ እንዲሁም ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያበረከተው እውቅና እና የዓለም አትሌቲክስ ቅርስ ለበለጠ ድል የሚያነሳሳ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የዓለም አትሌቲክስ ለሻምበል አትሌት አበበ ቢቂላ የ1960 የሮምና 1964 የቶኪዮ ኦሎምፒክ ድል እንዲሁም ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ እውቅና እና የዓለም አትሌቲክስ ቅርስን አበርክቷል። ሁለቱም እውቅናና የቅርስነት አርማ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም በክብር ተቀምጧል። እውቅናና የቅርስነት አርማውንም የዓለም አትሌቲክስ የቅርስ ዳይሬክተር ክሪስ ተርነር ያስረከቡ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ እና አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ተረክበውታል። የዓለም አትሌቲክስ ለሻምበል አበበ ቢቂላ እና ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሰጠው እውቅና በአትሌቲክስ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ላሳረፉ ታላላቅ ግለሰቦችና ሥፍራዎች የሚሰጠው 'የዓለም አትሌቲክስ የቅርስ ሰሌዳ' (World Athletics Heritage Plaque) ነው። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፤ አትሌቲክስ ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ከፍ ብላ እንድትታይ ማድረጉን ተናግረዋል። አትሌት አበበ ቢቂላ የኦሎምፒክ ድል የስፖርት ስኬት ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ትልቅ የኩራትና የነጻነት ምልክት መሆኑንም ከንቲባ አዳነች ገልጸዋል። ሻምበል አትሌት አበበ ቢቂላ በ1952 የሮም ኦሎምፒክ በባዶ እግሩ በማሸነፍ አፍሪካንና የጥቁር ሕዝቦችን ያኮራ መሆኑን አስታውሰው፤ በ1956 የቶኪዮ ኦሎምፒክ ድሉን በመድገም ድንቅ ስኬት ማስመዝገቡን ገልጸዋል። የእርሱን ፈለግ በመከተልም በርካታ አትሌቶች በዓለም አደባባይ ድል በማድረግ የኢትዮጵያን ዓርማ በክብር ከፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የመዲናዋ ሌላኛው ድምቀት እና በርካታ ሰዎች የሚያሳትፍ መሆኑን ጠቁመው፤ ለሁለቱም እውቅናና ክብር የተሰማቸውን ደስታም ገልጸዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ ፤ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዳዲስ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአትሌቲክስ ዘርፍ የገነባችውን መልካም ዝና ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በማስቀጠል ላይ የሚገኝ መሆኑን ጠቁመው፣ በተሳታፊ ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚው መሆኑንም ተናግረዋል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለሕዝቦች የአብሮነት እሴት መጎልበት ትልቅ ትርጉም እያበረከተ መሆኑን ጠቁመው፤ እውቅናው ለበለጠ ድል የሚያነሳሳ መሆኑንም አክለዋል። የዓለም አትሌቲክስ የቅርስ ዳይሬክተር ክሪስ ተርነር፤ የዓለም አትሌቲክስ ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የቅርስነት ሰሌዳ ሽልማትን ሲያበረክት ደስታ ይሰማዋል ብለዋል፡፡ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከታላላቅ የአፍሪካ ስፖርታዊ ስኬቶች አንዱ መሆኑንም አክለዋል፡፡ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መስራች ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ለተሰጠው እውቅናና ሽልማት ምስጋናውን አቅርቧል። ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የተሰጠው እውቅናና ክብር በአፍሪካ መጀመሪያው ነውም ተብሏል።
ፖለቲካ
የማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም የኢትዮጵያ ቆይታቸውን አጠናቀው ተሸኙ
Nov 20, 2025 132
አዲስ አበባ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-የማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በኢትዮጵያ የነበራቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አጠናቀው ተመልሰዋል፡፡ ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ልዑካቸው የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደማቅ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል፡፡ የማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለቱን ሀገራት ሁሉን አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ትብብሮችን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጥልቅ አጋርነት በሚያጠናክሩ በቱሪዝም፣ በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት እና ጤና ዘርፎች የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ከዚህም ባሻገር ስምምነቱ በኳራ ላምፑር ከተማ ምክር ቤትና የአዲስ አበባ አስተዳደር መካከል ትብብር መፍጠር በሚያስችሉ መስኮች ላይም ያተኮረ ነበር፡፡ የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም በኢትዮጵያ ቆይታቸው የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በተካሄደው የኢትዮ-ማሌዥያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሳትፈዋል። የኢትዮጵያ ጉብኝታቸው የኢትዮ-ማሌዥያ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ወደላቀ የኢኮኖሚ ትብብር ለማሸጋገር ወሳኝ ሚና እንዳለውም አረጋግጠዋል፡፡ የሩቅ ምስራቋ እሲያዊት ሀገር ማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም የቀናት ኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በመከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፎች በጋራ ለመሥራት በሚያስችላቸው ጉዳይ ላይ መከሩ
Nov 20, 2025 106
አዲስ አበባ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያና አዘርባጃን በመከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፎች በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የሁለትዮች የጋራ ውይይት አድርገዋል፡፡ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) እና በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በሁለትዮሽ በትብብር በሚሠሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በውይይታቸው ላይም ፥ኢትዮጵያ የመከላከያ-ኢንዱስትሪ መሠረተ ልማቷን ለማጠናከር ትኩረት ሰጥታ እየሠራች መሆኑን ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) አስረድተዋል። ሁለቱ ሀገሮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ኢትዮጵያ ቁርጠኛ ናት ማለታቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ አመላክቷል። ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ በበኩላቸው፣ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል። ሀገራቸው ኢትዮጵያን የመከላከያ ኢንዱስትሪ አጋሯ ለማድረግ ፍላጎት እንዳላትም ጠቁመዋል።
በክልሉ ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከል የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት የማስጠበቁ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል
Nov 20, 2025 106
ጎንደር፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከልና የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት የማስጠበቁ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገለጸ። ከጎንደር ቀጣና ለተውጣጡ የፖሊስ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ስልጠና በጎንደር ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ በስልጠናው መድረክ ላይ በክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የአስተዳደርና ልማት ጠቅላይ መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር አያልነህ ተስፋዬ ባደረጉት ንግግር ፤ የክልሉ ፖሊስ አመራርና አባላቱ ለክልሉ ሰላምና የሕግ የበላይነት መከበር ዋጋ መክፈላቸውን አስታውሰዋል። በዚህም ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ጠቁመው፤ ወንጀል ከመፈፀሙ በፊት አስቀድሞ በመከላከልና የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት ማስጠበቅ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በፖሊስ ተቋሙ በርካታ የሪፎርም ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፤ ሪፎርሙም ተቋማዊ የአስተሳሰብና የአመለካከት አንድነትን ለማምጣት ወሳኝ እርምጃ ነው ብለዋል። ሪፎርሙን መሰረት አድርጎ የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናም በአግባቡ በመከታተል በቀጣይ ሃላፊነታቸውን በላቀ ብቃት እንዲወጡ ለማስቻል የተመቻቸ መሆኑን አስረድተዋል። በፈጣንና ተለዋዋጭ ዓለም ዘመኑ የሚጠይቀውን ፖሊሳዊ እውቀት መሰረት ያደረገ አደረጃጀትና መዋቅር ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው፡፡ የፖሊስ አመራርና አባላትን ተግባርና ሀላፊነታቸወን በብቃት እንዲወጡ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ በበኩላቸው፤ የሕግ የበላይነት በማረጋጋጥ የወንጀል ድርጊቶችን በመቆጣጠር ረገድ የፖሊስ መዋቅሩ ተሳትፎና ትብብር ውጤት እንዲመጣ አግዟል ብለዋል። በቀጣይ የላቅ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ሪፎርሙን ወደ ተግባር በማሸጋገር የሕዝብን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማጎልበት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል። ለአንድ ሳምንት በሚቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ላይ ከጎንደር ከተማ፣ ከማዕከላዊ፣ ከሰሜንና ከምዕራብ ጎንደር ዞኖች የተውጣጡ ከፍተኛና መካከለኛ የፖሊስ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡
የህዝብ የሰላም ዘብ በመሆን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሚሰራ ጠንካራ የፖሊስ ኃይል የመገንባት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Nov 20, 2025 96
ባሕርዳር፤ ሕዳር 11/2018 (ኢዜአ)፡- የህዝብ የሰላም ዘብ በመሆን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሚሰራ ጠንካራ የፖሊስ ኃይል የመገንባት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። ለዋና ጠቅላይ መምሪያው የፖሊስ አመራሮችና ከፍተኛ መኮንኖች የአቅም ግንባታ ስልጠና በባሕርዳር ከተማ እየሰጠ ነው። በክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ታደሰ አያሌው፤ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ንግግር ወንጀልን በመከላከል፣ ሰላምን በማፅናት፣ የሕግ የበላነትን ለማረጋገጥ በቴክኖሎጅ እውቀት የዳበረ ተቋማዊ አመራር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ሕዝቡ የሰላም ዘብ በመሆን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሚሰራ ጠንካራ የፖሊስ ኃይል የመገንባት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የስልጠናውም ዓላማ የፖሊስ ሪፎርም አተገባበርን አጠናክሮ በማስቀጠል የዘላቂ ሰላም ግንባታና የወንጀል መከላከል ስራን ለማጎልበት መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት በተለይም አመራሩ የላቀ የአመራር ጥበብ፣ የቴክኖሎጂ እና የካበተ እውቀት የሚያስፈልገው በመሆኑ በዚሁ ልክ መዘጋጀት የግድ መሆኑን ተናግረዋል። የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ የክልሉ የፀጥታ ኃይል ከመከላከያ ሰራዊት ጎን በመሰለፍ ሰላሙ ፀንቶ እንዲቀጥልና ልማቱ እንዲፋጠን ሌት ተቀን ተግቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም ስልጠናው በየደረጃው ያለው የፖሊስ አመራር በተናበበና በተቀናጀ አግባብ ለተልዕኮው በላቀ ለመወጣት የሚያዘጋጅ በመሆኑ በትኩረት መከታተል እንደሚገባ ተናግረዋል።
በብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የተመራ የልዑካን ቡድን ከጅቡቲ አቻው ጋር ውጤታማ ውይይት አደረገ
Nov 19, 2025 211
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ ዛሬ ረፋድ ላይ ጅቡቲ የገባው በብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የተቋሙ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላን ያካተተው የልዑካን ቡድን ከጅቡቲ አቻው ጋር የደኅንነት ትብብሮችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውጤታማ ውይይት አደረገ። ውይይቱ የሁለትዮሽ ግንኙነትን፣ ቀጣናዊ የደህንነት ትብብሮችን እና ተያያዥ ጉዳዮችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
አመራሩ በመፍጠር እና በመፍጠን ለልማትና ለህዝብ ተጠቃሚነት ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል
Nov 19, 2025 147
አሶሳ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በየደረጃው ያለው አመራር በመፍጠር እና በመፍጠን ለሀገር ልማትና ለህዝብ ተጠቃሚነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር ተናገሩ። ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል በተለይም የአመራሩ ብቃትና ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በየደረጃው ያለው አመራር በመፍጠር እና በመፍጠን ለሀገር ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት የበለጠ ለመስራት ሊዘጋጅ እንደሚገባ አስገንዝበው የስልጠናው አላማም ይሄው ነው ብለዋል። በስልጠናው የግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ የቱሪዝም፣ የከተማ ልማት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶችን ለማስቀጠል የዳበረ ውይይት የሚደረግበት መሆኑንም ተናግረዋል። በስልጠናው ተሞክሮዎችና ልምዶችን በመጋራት አመራሩ በጋራ ለላቀ ስኬት ለመስራት የሚዘጋጅበት ስለመሆኑም ገልጸዋል። የአመራሮቹ ስልጠና ለተከታታይ ስምንት ቀናት የሚሰጥ መሆኑም ታውቋል።
አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነትን እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጠናከር አለበት
Nov 19, 2025 126
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የአመራሩን የአስተሳሰብ አንድነት እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሠራ በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሞገስ ባልቻ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ የአመራር አባላት ስልጠና በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በስልጠናው የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛና መካከለኛ አመራር አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ ስልጠናው “በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ ለሚቀጥሉት ስምንት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል። በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሞገስ ባልቻ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ገለጻ፤ የአመራሩን የአስተሳሰብ አንድነት እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት ይሠራል ብለዋል። አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነትን እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጠናከር እንደሚገባውን ተናግረዋል። የስልጠናው ዓላማም በአመራሩ መካከል የበለጠ መቀራረብና የአስተሳሰብ አንድነትን መፍጠር እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጎልበት መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም አገልጋይና ሁለገብ የሆነ አመራር መፍጠር ከስልጠናው ዓላማዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ ስልጠናው በተለያዩ ሀገራዊ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በማተኮር እንደሚሰጥም ተናግረዋል። በዚህም ስልጠናው በመደመር መንግስት እይታ የግብርና፣ የገጠር፣ የመዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ጉዞ፣ የኢንዱስትሪ እና የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ እንዲሁም የከተማ ልማት በሚል ርዕሶች ላይ እንደሚያተኩር ገልጸዋል፡፡ ስልጠናው የአመራሩን እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነባ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በስልጠናው ከሁለት ሺህ በላይ የፌዴራልና የከተማዋ ከፍተኛና መካከለኛ አመራር አባላት እንደሚሳተፉና ጎን ለጎንም የተግባርና የመስክ የልማት ስራ ጉብኝቶች እንደሚከናወኑ ተገልጿል።
የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን- የፖሊስ አባላት
Nov 19, 2025 134
ቦንጋ፤ ህዳር 10/2018 (ኢዜአ)፦ የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፖሊስ አመራርና አባላት ተናገሩ። በክልሉ "ከጂኦ ስትራቴጂካዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሃሳብ በየደረጃው ለሚገኙ የፖሊስ አመራርና አባላት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል። በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የፖሊስ አመራርና አባላትም የተሰጠው ስልጠና በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት ህዝብን ከማገልገል ባለፈ በሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የተሻለ ግንዛቤ ለመያዝ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል። ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል ኮማንደር እታለማው ተፈራ፣ ኢንስፔክተር አባይነህ አልዬ እና ምክትል ኢንስፔክተር አንድነት አበራ፤ የተሰጠው ስልጠና ወቅታዊ ሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮችን በመረዳት ለላቀ ህዝባዊ አገልግሎት የሚያዘጋጅ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህም ባለፈ ወቅታዊ ሁኔታዎችን በአግባቡ በመረዳት በዚሁ ልክ የፓሊስ አባላት አቅማችንን ማሳደግ ያለብን መሆኑን የተገነዘብንበት ነው ብለዋል። በሁሉም መስኮች እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ከምንም በላይ የህዝብን ሰላም ማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አንስተው ለዚህም የፖሊስ አባላት የላቀ ሃላፊነት ይጠበቅብናል ለዚህም ተዘጋጅተናል ሲሉ ተናግረዋል። የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን በማለትም አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ የፖሊስ አባላት የህዝብና የሀገር ወገንተኝነታቸውን በተግባር በማሳየት ለሰላምና ለልማት ዘብ መቆም እንዳለባቸው ገልጸዋል። በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተመዘገበው ስኬት ውስጥ የፖሊስ ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተው በቀጣይም ይህንኑ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ ሀገር በመገንባት ሂደት በየሙያ መስኩ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አንስተው የፖሊስ አባላት የክልሉን ሰላምና ልማት በዘላቂነት ለማስቀጠል እንዲተጉ አሳስበዋል። የክልሉ መንግስት የፖሊስን አቅም በቴክኖሎጂ እና በስልጠና ጭምር ለማጠናከር የሚሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ለሶስት ተከታታይ ቀናት በተሰጠው ስልጠና ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተሞች የተወጣጡ የፖሊስ አባላትና አመራሮች ተሳትፈዋል።
ፖለቲካ
የማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም የኢትዮጵያ ቆይታቸውን አጠናቀው ተሸኙ
Nov 20, 2025 132
አዲስ አበባ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-የማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በኢትዮጵያ የነበራቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አጠናቀው ተመልሰዋል፡፡ ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ልዑካቸው የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደማቅ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል፡፡ የማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለቱን ሀገራት ሁሉን አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ትብብሮችን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጥልቅ አጋርነት በሚያጠናክሩ በቱሪዝም፣ በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት እና ጤና ዘርፎች የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ከዚህም ባሻገር ስምምነቱ በኳራ ላምፑር ከተማ ምክር ቤትና የአዲስ አበባ አስተዳደር መካከል ትብብር መፍጠር በሚያስችሉ መስኮች ላይም ያተኮረ ነበር፡፡ የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም በኢትዮጵያ ቆይታቸው የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በተካሄደው የኢትዮ-ማሌዥያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሳትፈዋል። የኢትዮጵያ ጉብኝታቸው የኢትዮ-ማሌዥያ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ወደላቀ የኢኮኖሚ ትብብር ለማሸጋገር ወሳኝ ሚና እንዳለውም አረጋግጠዋል፡፡ የሩቅ ምስራቋ እሲያዊት ሀገር ማሌዥያ ፌዴሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም የቀናት ኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በመከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፎች በጋራ ለመሥራት በሚያስችላቸው ጉዳይ ላይ መከሩ
Nov 20, 2025 106
አዲስ አበባ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያና አዘርባጃን በመከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፎች በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የሁለትዮች የጋራ ውይይት አድርገዋል፡፡ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) እና በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በሁለትዮሽ በትብብር በሚሠሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በውይይታቸው ላይም ፥ኢትዮጵያ የመከላከያ-ኢንዱስትሪ መሠረተ ልማቷን ለማጠናከር ትኩረት ሰጥታ እየሠራች መሆኑን ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) አስረድተዋል። ሁለቱ ሀገሮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ኢትዮጵያ ቁርጠኛ ናት ማለታቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ አመላክቷል። ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ በበኩላቸው፣ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል። ሀገራቸው ኢትዮጵያን የመከላከያ ኢንዱስትሪ አጋሯ ለማድረግ ፍላጎት እንዳላትም ጠቁመዋል።
በክልሉ ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከል የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት የማስጠበቁ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል
Nov 20, 2025 106
ጎንደር፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከልና የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት የማስጠበቁ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገለጸ። ከጎንደር ቀጣና ለተውጣጡ የፖሊስ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ስልጠና በጎንደር ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ በስልጠናው መድረክ ላይ በክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የአስተዳደርና ልማት ጠቅላይ መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር አያልነህ ተስፋዬ ባደረጉት ንግግር ፤ የክልሉ ፖሊስ አመራርና አባላቱ ለክልሉ ሰላምና የሕግ የበላይነት መከበር ዋጋ መክፈላቸውን አስታውሰዋል። በዚህም ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ጠቁመው፤ ወንጀል ከመፈፀሙ በፊት አስቀድሞ በመከላከልና የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት ማስጠበቅ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በፖሊስ ተቋሙ በርካታ የሪፎርም ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፤ ሪፎርሙም ተቋማዊ የአስተሳሰብና የአመለካከት አንድነትን ለማምጣት ወሳኝ እርምጃ ነው ብለዋል። ሪፎርሙን መሰረት አድርጎ የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናም በአግባቡ በመከታተል በቀጣይ ሃላፊነታቸውን በላቀ ብቃት እንዲወጡ ለማስቻል የተመቻቸ መሆኑን አስረድተዋል። በፈጣንና ተለዋዋጭ ዓለም ዘመኑ የሚጠይቀውን ፖሊሳዊ እውቀት መሰረት ያደረገ አደረጃጀትና መዋቅር ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው፡፡ የፖሊስ አመራርና አባላትን ተግባርና ሀላፊነታቸወን በብቃት እንዲወጡ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ በበኩላቸው፤ የሕግ የበላይነት በማረጋጋጥ የወንጀል ድርጊቶችን በመቆጣጠር ረገድ የፖሊስ መዋቅሩ ተሳትፎና ትብብር ውጤት እንዲመጣ አግዟል ብለዋል። በቀጣይ የላቅ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ሪፎርሙን ወደ ተግባር በማሸጋገር የሕዝብን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማጎልበት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል። ለአንድ ሳምንት በሚቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ላይ ከጎንደር ከተማ፣ ከማዕከላዊ፣ ከሰሜንና ከምዕራብ ጎንደር ዞኖች የተውጣጡ ከፍተኛና መካከለኛ የፖሊስ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡
የህዝብ የሰላም ዘብ በመሆን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሚሰራ ጠንካራ የፖሊስ ኃይል የመገንባት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Nov 20, 2025 96
ባሕርዳር፤ ሕዳር 11/2018 (ኢዜአ)፡- የህዝብ የሰላም ዘብ በመሆን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሚሰራ ጠንካራ የፖሊስ ኃይል የመገንባት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። ለዋና ጠቅላይ መምሪያው የፖሊስ አመራሮችና ከፍተኛ መኮንኖች የአቅም ግንባታ ስልጠና በባሕርዳር ከተማ እየሰጠ ነው። በክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ታደሰ አያሌው፤ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ንግግር ወንጀልን በመከላከል፣ ሰላምን በማፅናት፣ የሕግ የበላነትን ለማረጋገጥ በቴክኖሎጅ እውቀት የዳበረ ተቋማዊ አመራር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ሕዝቡ የሰላም ዘብ በመሆን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሚሰራ ጠንካራ የፖሊስ ኃይል የመገንባት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የስልጠናውም ዓላማ የፖሊስ ሪፎርም አተገባበርን አጠናክሮ በማስቀጠል የዘላቂ ሰላም ግንባታና የወንጀል መከላከል ስራን ለማጎልበት መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት በተለይም አመራሩ የላቀ የአመራር ጥበብ፣ የቴክኖሎጂ እና የካበተ እውቀት የሚያስፈልገው በመሆኑ በዚሁ ልክ መዘጋጀት የግድ መሆኑን ተናግረዋል። የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ የክልሉ የፀጥታ ኃይል ከመከላከያ ሰራዊት ጎን በመሰለፍ ሰላሙ ፀንቶ እንዲቀጥልና ልማቱ እንዲፋጠን ሌት ተቀን ተግቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በመሆኑም ስልጠናው በየደረጃው ያለው የፖሊስ አመራር በተናበበና በተቀናጀ አግባብ ለተልዕኮው በላቀ ለመወጣት የሚያዘጋጅ በመሆኑ በትኩረት መከታተል እንደሚገባ ተናግረዋል።
በብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የተመራ የልዑካን ቡድን ከጅቡቲ አቻው ጋር ውጤታማ ውይይት አደረገ
Nov 19, 2025 211
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ ዛሬ ረፋድ ላይ ጅቡቲ የገባው በብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የተቋሙ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላን ያካተተው የልዑካን ቡድን ከጅቡቲ አቻው ጋር የደኅንነት ትብብሮችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውጤታማ ውይይት አደረገ። ውይይቱ የሁለትዮሽ ግንኙነትን፣ ቀጣናዊ የደህንነት ትብብሮችን እና ተያያዥ ጉዳዮችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
አመራሩ በመፍጠር እና በመፍጠን ለልማትና ለህዝብ ተጠቃሚነት ጠንክሮ መስራት ይጠበቅበታል
Nov 19, 2025 147
አሶሳ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በየደረጃው ያለው አመራር በመፍጠር እና በመፍጠን ለሀገር ልማትና ለህዝብ ተጠቃሚነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር ተናገሩ። ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል በተለይም የአመራሩ ብቃትና ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በየደረጃው ያለው አመራር በመፍጠር እና በመፍጠን ለሀገር ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት የበለጠ ለመስራት ሊዘጋጅ እንደሚገባ አስገንዝበው የስልጠናው አላማም ይሄው ነው ብለዋል። በስልጠናው የግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ የቱሪዝም፣ የከተማ ልማት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶችን ለማስቀጠል የዳበረ ውይይት የሚደረግበት መሆኑንም ተናግረዋል። በስልጠናው ተሞክሮዎችና ልምዶችን በመጋራት አመራሩ በጋራ ለላቀ ስኬት ለመስራት የሚዘጋጅበት ስለመሆኑም ገልጸዋል። የአመራሮቹ ስልጠና ለተከታታይ ስምንት ቀናት የሚሰጥ መሆኑም ታውቋል።
አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነትን እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጠናከር አለበት
Nov 19, 2025 126
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የአመራሩን የአስተሳሰብ አንድነት እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሠራ በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሞገስ ባልቻ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ የአመራር አባላት ስልጠና በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በስልጠናው የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛና መካከለኛ አመራር አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ ስልጠናው “በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ ለሚቀጥሉት ስምንት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል። በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሞገስ ባልቻ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ገለጻ፤ የአመራሩን የአስተሳሰብ አንድነት እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት ይሠራል ብለዋል። አመራሩ የአስተሳሰብ አንድነትን እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጠናከር እንደሚገባውን ተናግረዋል። የስልጠናው ዓላማም በአመራሩ መካከል የበለጠ መቀራረብና የአስተሳሰብ አንድነትን መፍጠር እንዲሁም የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴትን ማጎልበት መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም አገልጋይና ሁለገብ የሆነ አመራር መፍጠር ከስልጠናው ዓላማዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ ስልጠናው በተለያዩ ሀገራዊ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በማተኮር እንደሚሰጥም ተናግረዋል። በዚህም ስልጠናው በመደመር መንግስት እይታ የግብርና፣ የገጠር፣ የመዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ጉዞ፣ የኢንዱስትሪ እና የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ እንዲሁም የከተማ ልማት በሚል ርዕሶች ላይ እንደሚያተኩር ገልጸዋል፡፡ ስልጠናው የአመራሩን እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነባ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በስልጠናው ከሁለት ሺህ በላይ የፌዴራልና የከተማዋ ከፍተኛና መካከለኛ አመራር አባላት እንደሚሳተፉና ጎን ለጎንም የተግባርና የመስክ የልማት ስራ ጉብኝቶች እንደሚከናወኑ ተገልጿል።
የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን- የፖሊስ አባላት
Nov 19, 2025 134
ቦንጋ፤ ህዳር 10/2018 (ኢዜአ)፦ የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፖሊስ አመራርና አባላት ተናገሩ። በክልሉ "ከጂኦ ስትራቴጂካዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሃሳብ በየደረጃው ለሚገኙ የፖሊስ አመራርና አባላት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል። በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የፖሊስ አመራርና አባላትም የተሰጠው ስልጠና በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት ህዝብን ከማገልገል ባለፈ በሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የተሻለ ግንዛቤ ለመያዝ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል። ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል ኮማንደር እታለማው ተፈራ፣ ኢንስፔክተር አባይነህ አልዬ እና ምክትል ኢንስፔክተር አንድነት አበራ፤ የተሰጠው ስልጠና ወቅታዊ ሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮችን በመረዳት ለላቀ ህዝባዊ አገልግሎት የሚያዘጋጅ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህም ባለፈ ወቅታዊ ሁኔታዎችን በአግባቡ በመረዳት በዚሁ ልክ የፓሊስ አባላት አቅማችንን ማሳደግ ያለብን መሆኑን የተገነዘብንበት ነው ብለዋል። በሁሉም መስኮች እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ከምንም በላይ የህዝብን ሰላም ማስጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አንስተው ለዚህም የፖሊስ አባላት የላቀ ሃላፊነት ይጠበቅብናል ለዚህም ተዘጋጅተናል ሲሉ ተናግረዋል። የህዝብን ሰላም በማስጠበቅና ለልማት ስራዎች ስኬታማነት በላቀ ዝግጅትና ቁርጠኝነት እንሰራለን በማለትም አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ የፖሊስ አባላት የህዝብና የሀገር ወገንተኝነታቸውን በተግባር በማሳየት ለሰላምና ለልማት ዘብ መቆም እንዳለባቸው ገልጸዋል። በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተመዘገበው ስኬት ውስጥ የፖሊስ ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተው በቀጣይም ይህንኑ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ ሀገር በመገንባት ሂደት በየሙያ መስኩ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አንስተው የፖሊስ አባላት የክልሉን ሰላምና ልማት በዘላቂነት ለማስቀጠል እንዲተጉ አሳስበዋል። የክልሉ መንግስት የፖሊስን አቅም በቴክኖሎጂ እና በስልጠና ጭምር ለማጠናከር የሚሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ለሶስት ተከታታይ ቀናት በተሰጠው ስልጠና ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተሞች የተወጣጡ የፖሊስ አባላትና አመራሮች ተሳትፈዋል።
ማህበራዊ
የኩላሊት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Nov 20, 2025 52
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የኩላሊት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የጤና ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ስር የሰደደ ኩላሊት በሽታን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል መርሃ ግብር አስጀምሯል። ሚኒስቴሩ መርሃ ግብሩን ያስጀመረው ከፖፕሌሽን ሰርቪስ ኢንተርናሽናል (ፒ ኤስ አይ ) እና አስትራዜኒካ ከተሰኙ መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ሲሆን ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት እንደሚተገበር ተገልጿል። መርሃ ግብሩ በጤና ጣቢያዎችና መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ስር ለሰደደ ኩላሊት በሽታ አጋላጭ የሆኑ ግፊት እና ስኳር በሽታዎችን ምርመራ በማድረግ መለየት እና ህክምና የሚሰጥበት ሥርዓት ያካተተ ነው። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ እንዳሉት፤በኢትዮጵያ ስር የሰደደ ኩላሊት ታማሚዎች ቁጥር ከ6 በመቶ በላይ ነው። ለዚህ ደግሞ ዋነኛ መንስኤ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል የደም ግፊትና ስኳር በሽታ እንደሚገኙበት ጠቁመው መሰል ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ ለመከላከል እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም ሚኒስቴሩ የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ አውጥቶ እየተገበረ መሆኑን ጠቁመው ዜጎች ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች አጋላጭ ከሆኑ የአኗኗር ዘይቤዎች ራሳቸውን እንዲጠበቁ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። አካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ስብ የበዛበትና ጤናማ ያልሆነ አመጋገብ አጋላጭ መሆኑን ጠቅሰው ህብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ ጨብጦ ራሱን እንዲጠብቅ እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። ሚኒስቴሩ ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን ይፋ ያደረገው መርሃ ግብር በጤና ጣቢያዎችና መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች የግፊትና ስኳር ምርመራ እና ልየታ የሚያደርጉ የጤና ባለሙያዎች አቅም መገንባት፣ለህክምና የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በሟማላት አገራዊ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል። ፖፕሌሽን ሰርቪስ ኢንተርናሽናል (ፒ ኤስ አይ ) የኢትዮጵያ ቢሮ ተጠባባቂ ተወካይ ሩት ወልደትንሳኤ በበኩላቸው፤ ስር የሰደደ የኩላሊት በሽታን በኢትዮጵያ ያለበትን ደረጃ ለማወቅ የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት መደረጉን ተናግረዋል። ጥናቱን መሰረት በማድረግም በቀጣይ የሚወሰዱ እርምጃዎች አቅጣጫዎች መቀመጡን አስረድተዋል። ስር ለሰደደ ኩላሊት በሽታ አጋላጭ የሆኑት ግፊትና ስኳር በሽታዎች ምርመራ የሚያደርጉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ሥልጠና እንደሚሰጡም አመልክተዋል። የኩላሊት ጤንነትን ለመጠበቅ የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ህብረተሰቡ የኩላሊት ጤና የሚያስጠብቅበት መንገዶች ላይ በዘመቻ መልክ ግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባራት እንደሚከናወኑም አስረድተዋል። ከሳሃራ በታች ያሉ አፍሪካ አገራት የአስትራዜኒካ ቢሮ ዳይሬክተር አሚት ባክሪ በበኩላቸው፤ አስትራ ዜኒካ "ሄልዚ ሀርት አፍሪካ" በተሰኘ መርሃ ግብር በኩል በአፍሪካ 77 ሚሊዮን አፍሪካዊያን የደም ግፊት ተጋላጭነት ምርመራ ማካሄዱን ተናግረዋል። ለ11 ሺህ 890 የጤና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠቱን ገልጸዋል። አስትራዜኒካ ሰፊ ልምድ አለው ያሉት ዳይሬክተሩ ስር የሰደደ የኩላሊት በሽታ አስቀድሞ መከላከል ላይ ከኢትዮጵያ ጋር በአጋርነት በመስራታችን ደስተኞች ነን ብለዋል።
መድኃኒቶችን በተላመዱ ጀርሞች ምክንያት የሚከሰቱ የጤና እክሎችን ለመከላከል የግሉ ዘርፍ አጋርነት ሊጎለብት ይገባል
Nov 20, 2025 63
አዲስ አበባ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-የጸረ ተዋህሲያ መድኃኒቶችን በተላመዱ ጀርሞች ምክንያት የሚከሰቱ የጤና እክሎችን ለመከላከል የግሉ ዘርፍ አጋርነት ሊጎለብት እንደሚገባ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ። የጤና ሚኒስቴር ዓለም አቀፍ የፀረ ተዋህሲያን መድሀኒቶች በጀርሞች መላመድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት እና አራተኛውን የአምስት ዓመት ሀገር አቀፍ የትግበራ ዕቅድ ማስጀመሪያ መርሀ ግብርን ባለድርሻ አካላትና አጋር አካላት በተገኙበት በይፋ አስጀምሯል። የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒቶች በበሽታ አምጪ ተህዋሲያን ሳቢያ በሰውና በእንስሳት ጤና ላይ የሚከሰቱ በሽታዎችን ለመከላከልና ለማከም የምንጠቀማቸው መድሀኒቶች ናቸው። ይሁን እንጂ ማህበረሰቡ የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒቶችን በአግባቡ ባለመጠቀሙ ጀርሞች የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒቶችን በመላመድ አደጋ እያስከተሉ መሆኑ በመርሀ ግብሩ ተገልጿል። የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚሁ ወቅት፤ የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒቶች በጀርሞች መላመድ ምክንያት በሰዎች ላይ የጤና ቀውስ እየፈጠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ በዚህም አምራች የሰው ሀይሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ፤ በሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገትና ምርታማነት የራሱ የሆነ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒቶች በጀርሞች መላመድ እያስከተለ ያለውን ችግር ለመፍታት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡ ጤና ሚኒስቴር በጀርሞች የተላመዱ ጸረ ተዋህሲያን መድሀኒቶችን በመለየት መፍትሄ ማምጣት የሚያስችሉ በላብራቶሪ የመመርመር አቅምን የማሳደግ ስራ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን አመላክተዋል። የጸረ ተዋህሲያ መድኃኒቶችን በተላመዱ ጀርሞች ምክንያት የሚከሰቱ የጤና እክሎችን ለመከላከል የግሉ ዘርፍ አጋርነት ሊጎለብት እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት የኢትየጵያ ተወካይ ዶክተር ቢጆይ ናምቢየር በበኩላቸው፤ የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒት በጀርሞች መላመድ በጣም አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒት በጀርሞች መላመድን ለመግታት እቅድ ነድፋ ወደ ተግባር መግባቷ የሚበረታታ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። በፋኦ የኢትዮጵያ ተወካይ ቸንጀራይ ንጃጉ በበኩላቸው፤ የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒት በጀርሞች መላመድ እያሳደረ ያለውን ማነቆ ለመፍታት ኢትዮጵያ የምትደርገውን ጥረት እንደግፋለን ብለዋል። የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ በበኩላቸው፤ የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒቶች በጀርሞች መላመድ እያስከተለ ያለውን ጉዳት ለመቀነስ የአካባቢን ንጽህና መጠበቅ ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል ። በዚህም ባለስልጣኑ ጽዱ ኢትዮጵያና ከአየር ብክለት የጸዳች ከተማን ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ፅዱ አካባቢን መፍጠር ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር አቅም እንደሚያጎለብት ገልጸዋል። የአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጂን ካሴያ፤ የጸረ ተዋህሲያን መድሀኒት በጀርሞች መላመድ እያስከተለ ያለውን ችግር ለመፍታት መሬት የወረደ ስራ መሰራት አለበት ብለዋል።
ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንተጋለን- የመንግስት ሠራተኞች
Nov 20, 2025 66
ደብረ ብርሃን፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡- ቀልጣፋ አገልግሎት ለሕብረተሰቡ በመስጠት እርካታን ለማረጋገጥ በየተሰማሩበት መስክ ተግተው እንደሚሰሩ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች ገለጹ። "አገልጋይና የሰላም ዘብ የመንግስት ሠራተኛ፤ ለሁለንተናዊ እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች ዛሬ ተወያይተዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች ውስጥ አቶ ዳዊት አሳምነው በሰጡት አስተያየት፤ በተሰማራንበት የሙያ መስክ ሕብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል ወቅቱ የሚጠይቀው ተግባር ነው ብለዋል። በተለይ ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ለመልካም አስተዳደር መስፈን የበለጠ በመትጋት ኃላፊነታቸውን እንወጣለን ሲሉ ገልጸዋል። ለዚህም ብልሹ አሰራሮችንና ሙሰናን በመታገል ሰላምን ለማፅናት ለሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እንደሚወጡ አስታውቀዋል። የዛሬው ውይይት ሠራተኛው የሕዝብ አገልጋይነትን በመላበስ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አሳምነው ወልደትንሳኤ ናቸው። የስራ ሰዓት ሳይሸራረፍ ተገልጋይን በቅንነት፣ በፍትሃዊነትና በታማኝነት በማገልገል እርካታን ለማረጋገጥ በመትጋት ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡም አክለዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት ፤ የመንግስት ሠራተኞች መደበኛ ተግባራቸውን ከማከናወን ባሻገር ለሰላም መከበር ተሳትፏቸውን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ከዚህ ቀደም ሰራተኛውና ነዋሪዎች በተቀናጀ አግባብ በመስራታቸው ሰላምን ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል። አሁን ላይ የተገኘውን ሰላም በማጽናት የአገልግሎት አሰጣጥ መዛነፎችን በማስተካከል የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ዛሬ የተዘጋጀው የውይይት መድረክም የመንግስት ሠራተኞች ዘመኑ የሚጠይቀውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ፈጣንና ውጤታማ አገልግሎት ለሕብረተሰቡ እንዲሰጡ የሚያግዝ መሆኑንም አስረድተዋል። በውይይቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ ተቋማት የመንግስት ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል።
የአርሶ አደሩን የአመጋገብ ስርዓት ለማሻሻል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Nov 20, 2025 105
አሶሳ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአርሶ አደሩን የአመጋገብ ስርዓት ለማሻሻል የሚያስችል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ከቆላማ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቡራሞ ወረዳ አምባ 14 ቀበሌ የበለፀገ ምግብ አዘገጃጀት መርሃ ግብር አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ በግብርና ሚኒስቴር የምግብና ስርዓተ ምግብ ጽሕፈት ቤት የምግብና የስርዓተ ምግብ ዴስክ ሃላፊ ያሬድ አዲሱ፤ አርሶ አደሩ ከማምረት በተጨማሪ ምርቱን በመጠቀም የበለፀገ የአመጋገብ ስርዓት እንዲከተል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከቆላማ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የአርሶ አደሩን የአመጋገብ ስርዓት ለማሻሻል የሚያስችል የተቀናጀ የግብርና አሰራር ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ ጎን ለጎን አርሶ አደሩ በምግብ ስርአት ሂደት ላይ ያለውን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ተናግረዋል። የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የሥርዓተ ፆታና ሥርዓተ ምግብ አማካሪ አቶ ደመና ለማ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እያከናወነ የሚገኘው የምግብ ስርዓት ተኮር የግብርና ስራ ውጤታማ እንዲሆን የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። አርሶ አደሩ የሚያገኘውን ምርት ለምግብነት በማዋል ጤናማ እና አምራች ቤተሰብ እንዲኖረው በየቀበሌው የሚገኙ የግብርና እና የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የሚሰጡት ትምህርት ወሳኝነት አለው ሲሉም ተናግረዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ፍቅሩ አቡን፤ አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን ለማረጋገጥ ከሚያገኘው ምርት የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝ በተለያዩ የንቅናቄ መድረኮች ላይ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በቀጣይም በአቡራሞ ወረዳ የተጀመረውን ተሞክሮ በሌሎች አካባቢዎች ለማስፋፋት ቢሮው ከፕሮጀክቱ ጋር በትብብር ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።
ኢኮኖሚ
የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የክብርና የኢኮኖሚ ነፃነት ጉዳይ ነው
Nov 20, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የአህጉሪቷ የክብርና የኢኮኖሚ ነፃነት ጉዳይ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ አዘጋጅነት የአፍሪካ ሀገራትን የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥን ዓላማ ያደረገ ዓለም አቀፍ ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፤ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የአህጉሪቷ የክብርና የኢኮኖሚ ነፃነት ጉዳይ ነው ብለዋል። የአህጉሪቷን ዜጎች የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረትም ከተረጂነት በመላቀቅ የማይበገር የግብርና ሥርዓት የመገንባት አካል መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያም በዘመናዊ የግብርና ሥርዓት ምርታማነትን በማሳደግ ቀጣይነት ያለው የምርት ተወዳዳሪነት ዕድገት እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በሜካናይዜሽን የእርሻ ሥርዓትን በመደበኛና መስኖ ግብርና ምርታማነት ግልጽ ስትራቴጂክ ዕቅድ ነድፋ እየሰራችበት መሆኗንም አብራርተዋል። በስንዴ ምርታማነት የተመዘገበው ዕድገትም ከጥገኝነት በመላቀቅ ለውጭ ገበያ ማቅረብ ያስቻለ ተጨባጭ ስኬት ማስመዝገብ እየተቻለ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በኢትዮ-ሩሲያ መካከልም በትብብር ላይ የተመሰረተ ረጅም ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ሥርዓት በሚያሻሽሉ ዘላቂና ስትራቴጂክ የልማትና ኢንቨስትመንት የትብብር መስኮች በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን አስረድተዋል። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተርኪሂን፤ ሩሲያ የአፍሪካን ልማትና ዕድገት በመደገፍ የአህጉሪቷ ጠንካራ አጋር ነች ብለዋል። በቀጣይም የአፍሪካን የግብርና ሥርዓት ለማዘመን በሚደረገው ጥረት ለአህጉሪቷ የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ያሉት አምባሳደሩ፤ ለዚህም ከራሷ አልፎ ለውጭ ገበያ ጭምር ለመትረፍ በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኗ የሚደነቅ ነው ብለዋል።
ቴሌብር የፋይናንስ ተደራሽነት እና አካታችነትን ለማስፋት አስችሏል
Nov 20, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ቴሌብር ተጠቃሚዎች በቀላሉ የፋይናንስ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ ተደራሽነትና አካታችነትን ለማስፋት ማስቻሉን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ኢትዮ ቴሌኮም ከአዋሽ ባንክ ጋር በመተባበር "ጥላ" የተሰኘ አዲስ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት በቴሌብር አማካኝነት አስጀምሯል። ይህ ትብብር የሀገሪቱን የፋይናንስ አካታችነት ለማስፋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ኢትዮ ቴሌኮም የሀገሪቷን ዲጂታል ኢትዮጵያ ራዕይ እውን ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል። ቴሌብርን በመጠቀም በቀላሉ የፋይናንስ አገልግሎት ማግኘት መቻሉን አመልክተው፤ ይህም ለተጠቃሚዎቹ ምቹ፣ ፈጣን እና ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ተደራሽነት እንዲሰፋ ማድረጉን አንስተዋል። ቴሌብር የቴክኖሎጂ አቅምን ከባንክ ተቋማት የፋይናንስ ልምድ ጋር የተጣመረበት መሆኑን ጠቅሰው፤ የፋይናንስ አገልግሎትን ወደ ህብረተሰቡ በስፋት እንዲደርስ እያደረገ እንደሚገኝም አብራርተዋል። ከአዋሽ ባንክ ጋር የተደረገው አጋርነትም ሁለቱ ተቋማት የየራሳቸውን ጥንካሬ ለሀገራዊ ልማት ለማዋጣት እንደሚያስችላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ አስረድተዋል። "ጥላ" ዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ምቹ፣ ፈጣን እና ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ አገልግሎት የበለጠ ለማስፋት እንደሚረዳ ተናግረዋል። የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፀሀይ ሽፈራው በበኩላቸው፤ "ጥላ" የባንኩን የዲጂታል ለውጥ ለማፋጠን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በቴሌብር በኩል የሚቀርቡት እንደ ማይክሮ ብድር (Micro Credit)፣ የሞባይል ቁጠባ (Mobile Saving) አገልግሎቶች ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው እና አነስተኛ ንግድ ለሚሰሩ ትልቅ ዕድል ይፈጥራሉ ብለዋል። በቀጣይም ሁለቱ ተቋማት ተጨማሪ አዳዲስ እና ፈጠራ ያላቸው የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማጠናከር እንደሚሰሩ ጠቁመዋል። "ጥላ" የፋይናንስ ዲጂታል አገልግሎት የቁጠባ፣ የግለሰብ ብድር፣ ለአነሰተኛ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ብድር እና የዲቫይስ ፋይናንስ አገልግሎቶች በአንድ ጥላ ስር ለመስጠት የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የንግዱ ማህበረሰብ እገዛውን ማጎልበት ይጠበቅበታል
Nov 20, 2025 63
ሀዋሳ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል የንግዱ ማህበረሰብ እገዛውን ማጎልበት እንደሚጠበቅበት የከተማው አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ። ሀዋሳን ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለንግድና ለቱሪዝም ተመራጭ ከተማ ለማድረግ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑም ተመላክቷል፡፡ ከንቲባው በከተማዋ ከሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ጋር በከተማዋ ነባራዊ ሁኔታና ቀጣይ የልማት ትኩረቶች ላይ ዛሬ መክረዋል። በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በሀዋሳ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የንግዱ ማህበረሰብ ድጋፍና እገዛውን ማጎልበት ይጠበቅበታል፡፡ ከተጀመሩ የለውጥ ሥራዎች አኳያ ከተሞች የሚመሩበት እሳቤ መቀየሩን ያነሱት ከንቲባ ጥራቱ፣ የዜጎችን ህይወት ለሚቀይሩና የኢኮኖሚ እድገትን ማዕከል ላደረጉ ተግባራት ትኩረት እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡ በሀዋሳ ከተማ የለውጥ ሂደት ውስጥ ፍጥነትና ፈጠራን በማከል ከተማዋን ለንግድና ለኢንቨስትመንት እንዲሁም ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል። ለዚህም የሀዋሳ ሐይቅና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶች፣ የተዘረጉ የመንገድ መሠረተ ልማቶች እንዲሁም እንግዳ ወዳድ ህዝቧ መልካም ዕድሎች መሆናቸውን ነው ከንቲባው ያመላከቱት። በከተማዋ እየተከናወነ ያለው የኮሪደርና ሌሎች የልማት ሥራዎችም ለሀዋሳ የተሻለ አቅም እንደሚፈጥሩ አንስተዋል፡፡ ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ የከተማ ዕድገት ሁሉንም ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በመረዳት ግብሩን በታማኝነትና በወቅቱ በመክፈል ማሕበራዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣና ለልማቱም መፋጠን ተሳትፎውን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ አባተ ኪሾ በሰጡት አስተያየት፤ እያደገ የመጣውን የህዝብን የልማት ፍላጎት ለማሟላት ግብራችንን በአግባቡ በመክፈል የሚጠበቅብንን እንወጣለን ብለዋል፡፡ ከአስተዳደሩ ጎን በመቆም የከተማዋን እድገት ለማፋጠን የድርሻቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን የተናገሩት አቶ ጌቱ ተካ የተባሉ ሌላው የንግዱ ማህበረሰብ አባል ፣ አስተዳደሩ አሰራርን ምቹ ለማድረግ የጀመረውን ስራ እንዲያጠናክር ጠይቀዋል። በውይይት መድረኩ በከተማዋ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡
በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ የመሰብሰብ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Nov 20, 2025 60
ደሴ ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በገቢ አሰባሰብ ሂደት ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ለልማት የማዋል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው ከአማራ ክልል ምክር ቤት ጋር በመተባበር በሚሻሻሉ የገቢ አዋጆች ዙሪያ ዛሬ በደሴ ከተማ መክሯል። በመድረኩ ላይ የቢሮው ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ ለመመለስ እየተሰራ ነው። ለዚህም ከግብር ከፋዩ ማሕበረሰብ ጋር በመወያየት፣ ህገ ወጥ ተግባራትን በመከላከል፣ ገቢ አሰባሰቡን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የክልሉን ገቢ ለማሳደግና ወጪን በራስ አቅም ለመሸፈን ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። የገጠር መሬት መጠቀሚያ ክፍያ፣ የግብርና ሥራዎች ግብር፣ የቴምብር ቀረጥ ክፍያ እና የኤክሳይዝ ታክስን የተመለከቱ አዋጆችን በማሻሻል የገቢ አቅምን ማጠናከርም እንዲሁ። በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው ውስጥ እስካሁን ድረስ ከ25 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አውስተው፤ ቀሪውን በቀጣይ ለመሰብሰብ የተጠናከረ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ በገቢ አሰባሰብ ሂደት ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ለልማት የማዋል ተግባሩም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መንገሻ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። በአማራ ክልል ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ አሊ ይማም በበኩላቸው፤ ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሥርዓት መተግበር እንደሚገባ አሳስበዋል። ለረጅም ጊዜ ሲሰራባቸው የነበሩ አዋጆችን ለማሻሻል፣ አዳዲስ የገቢ አማራጮችን ለማስፋትና ገቢን በፍትሀዊነት ለመሰብሰብ እየተከናወነ ያለው ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የደሴ ከተማ ሴት ነጋዴዎች ማህበር ፕሬዚዳንት ወይዘሮ እፀገነት ታደሰ ፤ የንግዱ ማሕበረሰብ በሰራው ልክ ግብሩን እንዲከፍል በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል። በመድረኩ ላይ የአማራ ክልል ምክር ቤት አባላት፣ የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች፣ አርሶ አደሮችና የሕግ ምሁራን ተሳትፈዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ለፈጠራ ስራዎች የተሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው
Nov 20, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት የፈጠራ ስራዎችን ለማበረታታት የሰጠው ትኩረት የልማት ስራዎችን በማገዝ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የተቋማት የስራ ሃላፊዎች ገለፁ። የኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት በማስመልከት ትናንት ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍና ስራ ፈጣሪዎች ተቀናጅተው እንዲሰሩ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በተመለከተ ውይይት ተደርጓል። ሳምንቱ የዘርፉ ተዋንያን ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤቶች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ለማበረታታት ያለመ መሆኑም ተገልጿል። በዚሁ ጊዜ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ፤ መንግስት የኢትዮጵያን የኢንተርፕርነርሺፕ ምኅዳር ለማስፋት በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት ሥነ-ምህዳሩን ማስፋት የሚያስችሉ ወሳኝ የአሰራርና የሪፎርም አጀንዎች በመቅረጽ ተግባራዊ ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም ስራ ፈጣሪዎች ከተለምዷዊ አሰራር ተላቀው ንቁ፣ ችግር ፈቺና የስራ ዕድል ፈጣሪ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶር) መንግስት የቴክኖሎጂ ስነ ምህዳሩን ለማስፋት የፖሊሲ፣ ስትራቴጂና የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ወደ ስራ መግባቱን አስታውቀዋል። በዚህም በቅርቡ የጸደቀው የስታርታፕ አዋጅ በዘርፉ ሲያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን በመቅረፍና አዳዲስ እድሎችን በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል ነው ያሉት። የዲጂታል መሰረተ ልማትን ለማስፋፋት በተደረጉ ጥረቶች የዳታ ቤዝና የኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ማዕከላት መገንባታቸውን ጠቅሰዋል። በተሰሩት የዲጂታል መሰረተ ልማት ስራዎች በመታገዝ ሀብት ማፍራት የጀመሩ ስታርታፖች እየተበራከቱ መምጣታቸው ለውጤታማነቱ ማሳያ ነው ብለዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በረከት ፍስሃፅዮን በበኩላቸው፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት መንግስት የጀመራቸው የልማት ስራዎች ውጤት ማስገኘታቸውን አስታውቀዋል። በልማት ስራዎች የግል ዘርፉ ሚና እየጨመረ እንዲሄድ እንዲሁም የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት ይሰራል ብለዋል ። የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት የአካዳሚክ ጉዳዮች ሃላፊ ገነነ አበበ(ዶ/ር) ኢንስቲትዩቱ ለፈጠራና ኢኖቬሽን፣ ችግሮችን ወደ ዕድል ለመቀየርና የማይበገር ሀገራዊ ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ የተለያየ ክህሎት ያላቸው ዜጎች እውቀታቸውን ወደ ተግባር የሚቀይሩበት ምህዳር በማዘጋጀትና ከፋይናንስ ተቋማት በማገናኘት ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ እንግልትን በማስቀረት ጊዜና ገንዘባችንን ቆጥቦልናል - ተገልጋዮች
Nov 20, 2025 81
ጅማ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ እንግልትን በማስቀረት ጊዜና ገንዘባቸውን እንደቆጠበላቸው የከተማዋ ተገልጋዮች ገለጹ። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ህዝቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ እያነሳቸው የሚገኙ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የተዘረጋ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ነው። አገልግሎት አሰጣጡን አስመልክተው ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ ተገልጋዮች መካከል አቶ ሞአዝ ጅሀድ በማእከሉ የተገኙት የግብር መለያ ቁጥር ለማውጣት መሆኑን ገልፀው በፍጥነት በመስተናገዳቸው ጊዜ ማትረፋቸውን ተናግረዋል። የተጀመረውን ቀልጣፋ አገልግሎት በማስቀጠል ተገልጋዮች ከአገልግሎቱ ያተረፉትን ጊዜ በልማት ላይ እንዲያውሉት የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ መረጃን በመፈለግ የሚባክንን ጊዜና የተንዛዛ አሰራርን ያሻሻለ መሆኑን የገለፁት ደግሞ ሌላኛዋ ተገልጋይ ወይዘሮ ኢንዲያ መሀመድ አሚን ናቸው። ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር ረጅም ቀጠሮን ከመስጠት በተጨማሪ አገልግሎቱን በፍጥነት ለማግኘት አዳጋች እንደነበረ አስታውሰው ባገኙት ቀልጣፋ መስተንግዶ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ወይዘሮ ካሚላ ጀማል በበኩላቸው የተጀመረው ዘመናዊና ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጥ መጠናከር እንዳለበት ጠቁመው ከመረጃ ዴስክ ሰራተኞች እስከ ባለሙያዎች ያለው ቅንጅታዊ አሰራር የተገልጋዩን እርካታ ማሳደጉን መስክረዋል። መንጃ ፍቃድ ለማደስ በአገልግሎት ማእከሉ የተገኘው ወጣት አስረስ ዮሀንስ፤ ዘመናዊ አሰራሩ ቀደም ሲል የነበረውን የተዛዛ አገልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ የቀየረው በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብሏል። የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ምክትል ስራ አስኪያጅ ጀማል ሳሊ እንዳሉት፤ ዘመናዊ አገልግሎቱ በሰለጠኑ ባለሙያዎችና በቴክኖሎጂ ተደግፎ በተሟላ ሁኔታ እየተሰጠ ነው። የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ በ25 መስሪያ ቤቶች ከ130 በላይ በሚሆኑ የተለያዩ የአገልግሎት አይነቶች በቴክኖሎጂ በማስደገፍ እየተሰጠ መሆኑንም አክለዋል። ይህም ብልሹ አሰራርን በማስቀረትና የተገልጋዩን የአገልግሎት እርካታ በማሳደግ ረገድ ተጨማሪ አቅም መፍጠሩንም አቶ ጀማል አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሳይበር ጥቃቶችን አስቀድሞ መመከት የሚያስችል አቅም እየፈጠረ ነው
Nov 20, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰነዘሩ የሳይበር ጥቃቶችን አስቀድሞ ለመመከት የሚያስችል ጠንካራአቅም በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡ ባንኩ የሳይበር ደህንነት ወርን ለሁለተኛ ጊዜ እያከበረ ይገኛል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክስኪውቲቭ ምክትል ፕሬዝዳንት ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል ልማት ትልቅ ትኩረት ሰጥቷል። ይህን ተከትሎም ባንኩ የ(2020 - 2025) የመጀመሪያ ምዕራፍ ዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቅቆ ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ ዲጂታል መር ስትራቴጂ (2025-2030) መሸጋገሩን ገልፀዋል። አሁን ላይ ከባንኩ ጠቅላላ ግብይት ውስጥ ከ90 በመቶ በላይ የሚከናወነው በዲጂታል መንገድ መሆኑን ጠቅሰው፤ የግብይት ስርዓቱን ደህንነት ለማስጠበቅ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንM አረጋግጠዋል። አቶ ኤፍሬም አክለውም የሳይበር ደህንነት አስተዳደርን እስከ ምክትል ፕሬዝዳንት ደረጃ በማሳደግ ባንኩ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው የፋይናንስ ተቋም መሆኑን ገልፀዋል። በተጨማሪም የሳይበር ደህንነት ክፍሎች በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ.አይ) የሚሠራ የዜሮ ትረስት ደህንነት ስትራቴጂ (Al-powered Zero Trust Security Strategy) መዘጋጀቱን አመልክተዋል። የሳይበር ጥቃትን መከላከል የአንድ አካል ብቻ ተግባር አለመሆኑን ጠቁመውም፤ የሚመለከታቸው አካላት ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሽፕ ስልጠናዎች ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤትና መፍትሔ እያስገኙ ነው
Nov 19, 2025 134
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሽፕ ስልጠናዎች ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤትና መፍትሔ እያስገኙ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ፡፡ የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት በማስመልከት የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው። ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት የዘርፉ ተዋንያን ንቁና ብቁ ተሳትፎ በማድረግ ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤቶች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ለማበረታታት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በዚሁ ጊዜ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ፤ መንግስት የኢትዮጵያን የኢንተርፕርነርሽፕ ምኅዳር ለማስፋት በከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታትም የኢንተርፕርነርሽፕ ሥነ-ምህዳሩን ማስፋት የሚያስችሉ የአሰራርና የተቋማት የሪፎርም አጀንዳ በመቅረጽ ወሳኝ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ኢንተርፕርነሪያል መንግስት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም ከባህላዊ የአሰራር ሥረዓት ጠባቂነት በመላቀቅ ንቁ፣ ችግር ፈቺ እና ዕድል ፈጣሪ መሆን እያስቻሉት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም መንግስት ውጤታማ የመፍጠንና መፍጠር የአገልግሎት ሥርዓትን በመዘርጋት ስኬት እየተመዘገበ እንደሚገኝ አንስተዋል። የመንግስትን የአሰራር ስርዓት በፈጠራ የታገዘ እንዲሆን የፐብሊክ ሰርቪስ ኢኖቬሽን ላቦራቶሪ በማቋቋም አገልግሎቶችን የማሳለጥ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከተቋቋመ ጀምሮም የኢንተርፕርነር ስልጠና አቅሞችን በማሳደግ በአንድ ጊዜ በርካታ ዜጎችን የማሰልጠን አቅም እየዳበረ መምጣቱን አስረድተዋል። ኢትዮጵያውያን ኢንተርፕርነሮችን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ብቁና ንቁ ተወዳዳሪ በማድረግ ሀገራቸውን ከድህነት የሚያወጡ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ማህበረሰብ አካል እንድትሆንም የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም ባለፈው ዓመት በተደረገው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ውድድር ላይ ኢትዮጵያ በ8ኛ ደረጃ ማጠናቀቅ አንዳስቻላት አስታውሰዋል። በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤትና መፍትሔ እያስገኙ መሆኑን ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት የፈጠራ አቅሞችን ማጎልበት የሚያስችል መድረክ ነው ብለዋል።
ስፖርት
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ ባንክ ጋር የአምስት ዓመት የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ
Nov 20, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ ባንክ ጋር የአምስት ዓመት የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 25ኛ ዓመት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ አትሌቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በኃይሌ ግራንድ ሆቴል ተከብሯል። ከዚህም ባሻገር የአሜሪካ ባንክ (Bank of America) ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር እ.ኤ.አ ከ2026 ጀምሮ ለአምስት ዓመት የሚያቆየውን የአጋርነት ስምምነት ተፈራርሟል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መስራች አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በዚህ ወቅት፤ ስምምነቱ ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር ሳይሆን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የተደረገ መሆኑን ገልጿል። የአሜሪካ ባንክ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ለማስፋት ወደ ኢትዮጵያ ስለመጣ ምስጋና አቅርቧል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 25ኛ ዓመት ከአሜሪካ ባንክ ጋር አጋርነት የተፈራረምንበት ትልቁ የደስታዬ ቀን ነው ብሏል። ስምምነቱ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያን አቅም ለማሳደግ ትልቅ የመሰረት ድንጋይ መሆኑንም ገልጿል። የአሜሪካ ባንክ ዓለም አቀፍ የገበያ ትብብር ኃላፊ ብራድ ሮዝ በበኩላቸው፤ የዓለም አሻራ ከሆነው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር ለአምስት ዓመታት ስለምንሰራ ኩራት ይሰማናል ብለዋል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አንድነትን የሚፈጥር፣ የኢኮኖሚ መነቃቃትን የሚያሳልጥ መሆኑንም ገልጸዋል።
እውቅናው ለበለጠ ድል የሚያነሳሳ ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Nov 20, 2025 79
አዲስ አበባ፤ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፡-የዓለም አትሌቲክስ ለሻምበል አትሌት አበበ ቢቂላ እንዲሁም ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያበረከተው እውቅና እና የዓለም አትሌቲክስ ቅርስ ለበለጠ ድል የሚያነሳሳ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የዓለም አትሌቲክስ ለሻምበል አትሌት አበበ ቢቂላ የ1960 የሮምና 1964 የቶኪዮ ኦሎምፒክ ድል እንዲሁም ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ እውቅና እና የዓለም አትሌቲክስ ቅርስን አበርክቷል። ሁለቱም እውቅናና የቅርስነት አርማ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም በክብር ተቀምጧል። እውቅናና የቅርስነት አርማውንም የዓለም አትሌቲክስ የቅርስ ዳይሬክተር ክሪስ ተርነር ያስረከቡ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ እና አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ተረክበውታል። የዓለም አትሌቲክስ ለሻምበል አበበ ቢቂላ እና ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሰጠው እውቅና በአትሌቲክስ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ላሳረፉ ታላላቅ ግለሰቦችና ሥፍራዎች የሚሰጠው 'የዓለም አትሌቲክስ የቅርስ ሰሌዳ' (World Athletics Heritage Plaque) ነው። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፤ አትሌቲክስ ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ከፍ ብላ እንድትታይ ማድረጉን ተናግረዋል። አትሌት አበበ ቢቂላ የኦሎምፒክ ድል የስፖርት ስኬት ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ትልቅ የኩራትና የነጻነት ምልክት መሆኑንም ከንቲባ አዳነች ገልጸዋል። ሻምበል አትሌት አበበ ቢቂላ በ1952 የሮም ኦሎምፒክ በባዶ እግሩ በማሸነፍ አፍሪካንና የጥቁር ሕዝቦችን ያኮራ መሆኑን አስታውሰው፤ በ1956 የቶኪዮ ኦሎምፒክ ድሉን በመድገም ድንቅ ስኬት ማስመዝገቡን ገልጸዋል። የእርሱን ፈለግ በመከተልም በርካታ አትሌቶች በዓለም አደባባይ ድል በማድረግ የኢትዮጵያን ዓርማ በክብር ከፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የመዲናዋ ሌላኛው ድምቀት እና በርካታ ሰዎች የሚያሳትፍ መሆኑን ጠቁመው፤ ለሁለቱም እውቅናና ክብር የተሰማቸውን ደስታም ገልጸዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ ፤ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዳዲስ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአትሌቲክስ ዘርፍ የገነባችውን መልካም ዝና ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በማስቀጠል ላይ የሚገኝ መሆኑን ጠቁመው፣ በተሳታፊ ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚው መሆኑንም ተናግረዋል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለሕዝቦች የአብሮነት እሴት መጎልበት ትልቅ ትርጉም እያበረከተ መሆኑን ጠቁመው፤ እውቅናው ለበለጠ ድል የሚያነሳሳ መሆኑንም አክለዋል። የዓለም አትሌቲክስ የቅርስ ዳይሬክተር ክሪስ ተርነር፤ የዓለም አትሌቲክስ ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የቅርስነት ሰሌዳ ሽልማትን ሲያበረክት ደስታ ይሰማዋል ብለዋል፡፡ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከታላላቅ የአፍሪካ ስፖርታዊ ስኬቶች አንዱ መሆኑንም አክለዋል፡፡ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መስራች ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ለተሰጠው እውቅናና ሽልማት ምስጋናውን አቅርቧል። ለታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የተሰጠው እውቅናና ክብር በአፍሪካ መጀመሪያው ነውም ተብሏል።
አዲስ አዳጊው ነጌሌ አርሲ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዘገበ
Nov 20, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሰባተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ነጌሌ አርሲ ከመመራት ተነስቶ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አህመድ ሁሴን በ83ኛው ደቂቃ አዳማ ከተማን መሪ ማድረግ ችሎ ነበር። ይሁንና ሮሆቦት ሰላሎ በ92ኛው እና ገብረመስቀል ዱባለ በ96ኛው ደቂቃ ያስቆጠሯቸው ግቦች ነጌሌ አርሲን ወሳኝ ሶሶት ነጥብ እንዲያገኝ አስችሎታል። አዲስ አዳጊው ነጌሌ አርሲ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን በማስመዝገብ በስድስት ነጥብ ደረጃውን ወደ 11ኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ሽንፈቱን ያስተናገደው አዳማ ከተማ በበኩሉ በዘጠኝ ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ የሰባተኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከመቀሌ 70 እንደርታ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወሳኝ ድል አስመዘገበ
Nov 20, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሰባተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሸገር ከተማን 4 ለ 2 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ዳግማዊት ሰለሞን በጨዋታ ሁለት በፍጹም ቅጣት ምት አንድ በድምሩ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርታለች። ሃና ሲሳይ ቀሪዋን ጎል ለኢትዮ ኤሌክትሪክ ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ዓይናለም አለማየሁ እና ሰናይ ኡራጎ ለሸገር ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ21 ነጥብ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል። ሸገር ከተማ በ15 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። የኢትዮ ኤሌክትሪኳ ዳግማዊት ሰለሞን በሊጉ ያስቆጠረቻቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 14 ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት መሪነቷን አጠናክራለች። ዛሬ በተደረገ ሌላኛው ጨዋታ ይርጋጨፌ ቡና ባህር ዳር ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል።
አካባቢ ጥበቃ
የመዲናዋ የወንዝ ዳር ልማቶች የወንዞች ደህንነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና እያበረከቱ ነው
Nov 20, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የተከናወኑት የወንዝ ዳር ልማቶች ከህዝብ መዝናኛነታቸው ባሻገር የወንዞች ደህንነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና መጫወታቸውን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ በአዲስ አበባ የፍሳሽ ማስወገጃዎችን ከወንዞች ጋር በማገናኘት ሲፈጠሩ በቆዩ ችግሮች ወንዞች ለብክለት ተጋልጠው ቆይተዋል፡፡ ይህም ወንዞቹ ለሰዎች፣ ለእንስሳትና ለዕፅዋት ጤንነትና ደህንነት ጥቅም ከመስጠት ይልቅ ስጋት እንዲሆኑ አድርጓቸው ቆይቷል፡፡ ይህን ተከትሎ በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት አድማሱን በማስፋት ወደ ወንዝ ዳርቻ ልማት በመሸጋገሩ የወንዞችን ደህንነት ማስጠበቅ ተችሏል፡፡ የወንዝ ዳር ፕሮጀክት መተግበር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የስጋት ምንጭ የነበሩት ወንዞች የመዝናኛ ማዕከል ሆነዋል፡፡ ኢዜአ በወንዝ ዳር ልማቶች በለሙ ቦታዎች ሲዝናኑ ያገኛቸው የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች እንደገለጹት ቦታዎቹ አማራጭ የእረፍት ማሳለፊያ ከመሆናቸው ባሻገር የከተማዋን ገጽታ ውብ አድርገውታል፡፡ አቶ መርሳ በቀለ በወንዞች ዳርቻ የተሰሩ የልማት ስራዎች ከዚህ ቀደም ለማየትም ሆነ በአካባቢው ለማለፍ አስቸጋሪ የነበሩ ቦታዎችን ውብና ጽዱ ያደረጉ ናቸው ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ ወንዞችን ከብክለት ነፃ በማድረግ ደህንነታቸው ተጠብቆ ለህዝብ መዝናኛነት እንዲውሉ ከማስቻል ባለፈ አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብና ጽዱ እንዳደረጓት ገልጸዋል፡፡ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ግርማዬ ፍስሃ በበኩላቸው፤ የከተማዋ ወንዞች የቆሻሻ መጣያ እንደነበሩ አስታውሰው፤ በዚህ ደረጃ ለምተው በመመልከታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ የልማት ስራው ወንዞቹንና በዙሪያቸው ያሉ አካባቢዎችን ውብና ፅዱ ከማድረግ ባሻገር ኢትዮጵያዊያን በአካባቢ ጥበቃ ያላቸውን ልምድና ክህሎት ያሳዩበት መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ ጋዲሳ ዋቅጅራናቸው፡፡ በኮሪደር ልማትና በወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች ለህፃናትና ወጣቶች የሚያገለግሉ ምቹ የሆኑ በርካታ መዝናኛዎች መገንባታቸውን የተናገሩት ወጣት ሰለሞን ዳዊት እና አብዲ መልካሙ ናቸው፡፡ መዝናኛ ቦታዎቹ ጊዜአችንን በአልባሌ ቦታ ከማሳለፍ ይልቅ በመልካም ድባብ በመታጀብ ንፁህ አየር እየወሰድን እንድንዝናና ዕድል ፈጥረውልናል ብለዋል፡፡ የልማት ስራዎቹ ከመዝናኛነት ባለፈ ህብረተሰቡ ስለ አካባቢ ጥበቃና እንክብካቤ ያለው ግንዛቤ እንዲጨምር የሚያስችሉ መሆናቸውን የገለጸው ወጣት ይታያል ደጋጋ ነው ፡፡
በክልሉ በክረምቱ ወራት ለተተከሉ ችግኞች በበጋው ወራት የሚደረገው እንክብካቤ ተጠናክሮ ቀጥሏል
Nov 20, 2025 68
ጋምቤላ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከቡ ስራ በበጋው ወራትም ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ገለፀ። የጋምቤላ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አንድሪው ቱት ለኢዜአ እንደገለፁት በክረምቱ ወራት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከቡ ስራ በበጋውም ወራት ተጠናክሮ ቀጥሏል። ህብረተሰቡ ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የጽድቀት መጠናቸው እንዲጨምር እንክብካቤ እንዲያደርግ ግንዛቤ መፈጠሩን አንስተዋል። በአረንጓዴ ዐሻራ የለሙ አካባቢዎች ወደ ቀደመ ይዞታቸው እንዲመለሱ የእንክብካቤና የጥበቃ ስራው እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብሩ የለሙ አካባቢዎችን በመጠበቅ ለስራ እድል ፈጠራ እንዲውሉ በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች መተላለፋቸውንም ተናግረዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ ልማቱ ከስራ ዕድል ፈጠራው ባለፈም የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራን በማሳደግ የአርሶና አርብቶ አደሩን ምርታማነት በመጨመር የምግብ ዋስትናን እያረጋገጠ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ለአብነትም ባለፉት ዓመታት የተተከሉት ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው የማንጎ፣ የፓፓያ፣ የሙዝና ሌሎች የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች የአርሶ አደሩን ህይወት መለወጥ መጀመራቸውን ገልፀዋል። በክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና አጠቃቀም ዳይሬክተር ኬት ሉል በበኩላቸው በክልሉ በክረምቱ ወራት በአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ እነዚህን ችግኞች ከእንስሳትና ከሰው ንክኪ እንዲሁም ከሰደድ እሳት በመጠበቅና ለመንከባከብ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ ለተግባራዊነቱ ስራ አጥ ዜጎችን በማደራጀት ችግኞችን በመንከባከብ ተግባር ላይ እንዲሰማሩ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ ባለፈው የክረምት ወራት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች የጽድቀት መጠንም 78 በመቶ መድረሱን አክለዋል፡፡
በአማራ ክልል የግሪሳ ወፍ በሰብል ላይ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተቻለ
Nov 19, 2025 119
ባሕርዳር/ ደሴ ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ሶስት ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተው የግሪሳ ወፍ በሰብል ላይ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በቢሮው የዕፅዋት ጥበቃ ባለሙያ አቶ አበበ አናጋው ፤ የግሪሳ ወፍ በክልሉ ሰሜን ሸዋ፣ ደቡብ ወሎና ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች መከሰቱን ለኢዜአ ተናግረዋል። ቢሮው ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከጥቅምት 8/2018 እስከ ሕዳር 6/2018 ዓ.ም ድረስ ባደረገው በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት በሰብል ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን አስታውቀዋል። የኬሚካል ርጭቱ ግሪሳ ወፉ በሚያድርባቸው በተለዩ 604 ሄክታር የሚሸፍን ቦታዎች በተካሄደው ርጭት የግሪሳ ወፍ መንጋን ማስወገድ መቻሉን ገልጸዋል። በርጭቱም 1 ሺህ 208 ሊትር ኬሚካል ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቁመው፤ በዚህም ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የለማ ሰብልን ከጉዳት መታደግ መቻሉን ባለሙያው አስረድተዋል። በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ደጀኔ ከበደ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ጅሌ ጥሙጋ እና ደዋጨፋ ወረዳዎች የግሪሳ ወፍ መንጋ ተከስቶ ነበር። የወፉን ማደሪያ ሥፍራ በመለየት ከ155 ሄክታር መሬት ላይ በተደረገ የአውሮፕላን ኬሚካል ርጭት በሰብል ላይ ጉዳት ሳይደርስ መከላከል መቻሉን ተናግረዋል። በደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ በበኩላቸው፤ በቃሉ ወረዳ የተከሰተውን የግሪሳ ወፍ በአውሮፕላን የታገዘ ኬሚካል ርጭት በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ተናግረዋል። አርሶ አደሩ የደረሰውን ሰብል በወቅቱ ፈጥኖ ከመሰብሰብ ባሻገር ተባይና የግሪሳ ወፍ ሲመለከት ፈጥኖ ለግብርና ባለሙያዎች መረጃ እንዲሰጥ መክረዋል።
አሳታፊ የደን አስተዳደር ስርዓት የተፈጥሮ ደኖችን ህልውና መጠበቅ አስችሏል
Nov 19, 2025 182
ሚዛን አማን፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ተግባራዊ የተደረገው አሳታፊ የደን አስተዳደር ስርአት የተፈጥሮ ደኖችን ህልውና መጠበቅ ያስቻለ መሆኑን የክልሉ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ገለጸ። በኢትዮጵያ ሰፊ የደን ሽፋን ካላቸው አካባቢዎች መካከል የሚጠቀሰው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሁለት በባዮስፌር ሪዘርቭ የተመዘገቡ ጥብቅ የተፈጥሮ ደኖች መገኛ ነው። የክልሉ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ለማ ገብረሚካኤል ለኢዜአ እንደገለጹት፤በክልሉ ከጥንት ጀምሮ ያለው የደን አጠባበቅ ባህል የደን ሃብቶችን መጠበቅ፣ ማልማትና መንከባከብ ያስቻለ እሴት ሆኖ ቀጥሏል። በክልሉ ውስጥ ከሚገኘው አጠቃላይ የደን ይዞታ ውስጥ ከ760 ሺ ሔክታር በላይ የሚያካልሉ ሁለት ደኖች በባዮስፌር ጥብቅ የደን ስፍራነት በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት የተመዘገቡ መሆኑን ተናግረዋል። በካፋና ሸካ ዞኖች የሚገኙ ደኖችን ለመጠበቅ የተቋቋሙ ከ500 በላይ አሳታፊ የደን አስተዳደር ማኅበራት ለደኖቹ ሕልውና መጠበቅ የጎላ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን አንስተው በቀጣይም የደኖቹን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ለማሳደግና የኢኮቱሪዝም ቀጣና ለማድረግ የሚሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። በሸካ ዞን የአንድራቻ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሠራዊት ቆጭቶ በበኩላቸው፤ አሳታፊ የደን አስተዳደር ጥበቃ ሥርዓት ከሸካቾ ብሔረሰብ ባህል ጋር የተሳሰረ የሃብት መጠበቂያ እሴት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በሥርአቱ ደን ከመጠበቅ ባሻገር ከዘርፉ ኢኮኖሚ በማመንጨት አካባቢውን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑበት መሆኑንም ተናግረዋል። በወረዳው የዮኪጭጪ ቀበሌ አሳታፊ ደን አስተዳደር ማህበር አባል አቶ ገብረሥላሴ ቶንዶሮ፤ ደንን መጠበቅ ከጥንት የወረስነው ባህል በመሆኑ የትኛውንም የደን ውጤት ያለ ፍቃድና ያለ አግባብ መቁረጥ አይቻልም ብለዋል። ደኑ በደን ክልልነት ከተመዘገበ በኋላም በአሳታፊ ደን አስተዳደር ተደራጅተው ለደኑ ጥበቃ ከማድረግ ጎን ለጎን በውስጡ ማርን ጨምሮ ኮሮሪማ፣ ጥምዝና ሌሎች የደን ውጤቶችን በማምረት እየተጠቀሙ መሆኑን ተናግረዋል። የደን ሃብት ጥበቃ የቀደሙት ያወረሱን ሀብታችን በመሆኑ ጠብቆ ለትውልድ የማስተላለፍ ግዴታ አለብን ያለው ደግሞ የዩቲ ቀበሌ የአሳታፊ ደን አስተዳደር ማኅበር አባል ወጣት ተካልኝ ተሰማ ነው። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የሚቆረጥ ዛፍ እንዳይኖር በአሳታፊ የደን አስተዳደር በወጣው የጥበቃ መርሐ ግብር መሠረት ደኑን እየጠበቀ መሆኑን ገልጿል። የአሳታፊ ደን አስተዳደር ማኅበር የአንድ ቀበሌ ነዋሪና በደን አካባቢ ያሉ አባወራ የህብረተሰብ ክፍሎችን በአባልነት ያቀፈ ሲሆን በደን ክልል ውስጥ ሕገ ወጥ ድርጊት እንዳይፈጸም በጥበቃ የሚከላከሉበት ሥርአት ነው። አሳታፊ የደን አስተዳደር ስርአት ዓላማውም የደን ሀብትን ዘላቂነት ማረጋገጥ፣ የብዝሃ ሕይወትን መጠበቅ፣ የካርበን ክምችትን መጨመር እንዲሁም በአካባቢው የሚኖሩ ማህበረሰቦችን ኑሮ ማሻሻል እና ከደን የሚገኘውን ጥቅም ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንዲያገኙ ማድረግ ነው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል። ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል። ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ለሱዳን ግጭት ዓለም አቀፍ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል- ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
Nov 19, 2025 215
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የሱዳን ግጭት ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቀናጀ ምላሽ እንዲሰጥ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ያዘጋጀው ሁለተኛ የሱዳን የልዩ ልዑኮች ፎረም ዛሬ በጅቡቲ ተካሄዷል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ተዋንያን ተሳትፈዋል። ፎረሙ በሱዳን ላለው ቀውስ የተቀናጀ መልስ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር የሱዳን ሰላም በሱዳናውያን የሚመራ፣ ቀጣናዊ ትብብር የተረጋገጠበት እና ዓለም በአንድ ድምጽ የሚደግፈው ሊሆን እንደሚገባ አመልክተዋል። በሱዳን ያለውን ግጭት ለማስቆም፣ ንጹሃን ዜጎችን ለመጠበቅ እና የኢጋድ ቀጣናን የተረጋጋ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ዋና ፀሐፊው ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን በሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደረስ፣ የሰብዓዊ እርዳታ መተላለፊያ እንዲከፈት እና ተአማኒነት ያለው የስልጣን ሽግግር እንዲኖር በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። ኢጋድ ሱዳናውያን በሀገራቸው ሰላም እና ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ክብራቸው እንዲጠበቅ ያላቸው መሻት እንዲሳካ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በመረጃው አመልክቷል።
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 533
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 671
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል። ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 199
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 354
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው። በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው። የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው። “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል። በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 422
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 589
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2157
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2381
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3265
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3357
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 1429
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 966
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6799
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5276
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
በጥምር ግብርና ስኬት ያስመዘገቡት አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ
Nov 14, 2025 318
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ - ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ጨዛ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ለዘመናት ባከናወኑት የግብርና ልማት ሥራ ኑሯቸው ከእጅ ወደ አፍ የዘለለ አልነበረም። ዛሬ ላይ ሆነው ያን ዘመንና ያሳለፉትን ዕድሜ ሲያስታውሱ ይቆጫሉ። በኋላ ቀር መንገድ ሲያከናውኑት ከነበረው የግብርና ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ መሆንም፤ ሀብት ማፍራትም ሳይችሉ ቀርተዋል። አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ይባላሉ። ከሰበሰቡት ሰብል ጎተራቸው ሳይጎድል፣ ከእንስሳት እርባታ ስራቸውም ጥገታቸው ሳትነጥፍ ማየት የዘውትር ህልማቸው ነበር። ለም መሬት ይዘው ምርታማ ባለመሆናቸው ሲቸገሩ፣ የሚሰራ ጉልበት ይዘው ማዕዳቸው እየጎደለ የጎልማሳነት ዕድሜ መባቻ ድረስ ችግር ሲፈራረቅባቸው ዓመታትን አሳልፈዋል። ይህ ፍላጎታቸው ሰምሮ፣ ጓሯቸው ለምቶ፣ ቤታቸው ሞልቶና ጥሪት አፍርተው የማየት ውጥናቸው ሳይሳካ ዓመታት ቢቆጠሩም ዛሬ ግን በጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ነገሮች ተቀይረዋል። የዓመታት ምኞታቸውን ማሳካት ጀምረዋል። ከስድስት ዓመታት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ለስኬት እንዲበቁ ከማድረግ ባለፈ በአካባቢያቸው አርአያ የሆኑ አርሶ አደር አድርጓቸዋል። የጥምር ግብርና ስራቸው ለዓመታት ከነበሩበት ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ በማውጣት ለአፍም ለኪስም ሆኗቸዋል። የመንግስት የልማት ትኩረት የሆነው ጥምር ግብርና በውስን መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅንጅት እንዲያለሙ እድል ፍጥሮላቸዋል። በዋናነት በሰብል፣ በእንሰት፣ በፍራፍሬና በእንስሳት እርባታ ላይ አተኩረው እየሰሩ ይገኛሉ። ይህም የአንዱ ክፍተት በሌላው እየተሞለ ውጤታማ ስላደረጋቸው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው። ለቤት ፍጆታ ብቻ ያመርቱ የነበረው የእንሰት ምርትን በማስፋፋት ችግኙንና ተረፈ ምርቱን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጭምር ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያመርቱት ገብስ ለሌሎች አርሶ አደሮች ምሳሌ መሆን ችለዋል። ዝርያቸው የተሻሻሉ ላሞችን ስለሚያረቡም ወተት ከማጀታቸው አይጠፋም። በጓሯቸው የሚያለሙትን አትክልትና ፍራፍሬ ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ፈጥረዋል። አርሶ አደሩ ከንብ ማነብ ሥራቸውም እንዲሁ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው። ከአካባቢው ስነምህዳር ምክንያት ብዙም ያልተለመደውን ቡና በመትከል ለፍሬ አብቅተዋል። የእሳቸውን ፈለግ የተከተሉ ሌሎች አርሶ አደሮችም ቡና ማልማት ጀምረዋል። በእጅ ያለን ሀብት ወደ ውጤት ለመቀየር ተግቶ መስራትና ጽናት ያስፈለጋል ያሉት አርሶ አደር ወልዴ፣ በግብርና ባለሙያዎች የተደረገላቸው ሙያዊ ድጋፍና የተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ለውጤታቸው ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የእርሻ ልማትና የእንስሳት እርባታውን በቅንጅት ማከናወናቸውም እንዲሁ። አርሶ አደር ወልዴ የዓመታት ቁጭታቸው ዛሬ መፍትሄ እያገኘ ነው። የጥምር ግብርና ሥራቸው በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉና ልጆቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እንዲያሳድጉ አስችሏቸዋል። መኖሪያ ቤትን ጨምሮ የተለያየ ሀብት ለማፍራት ምክንያት በመሆኑም ልማቱን አስፋፍቶ ለማከናወን አቅደዋል። አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ጭምር አርአያ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙራዱ ብሩ ናቸው። ቀደም ሲል በገብስ ምርት ላይ ብቻ አተኩረው ይሰሩ የነበረውን የግብርና ሥራ እንዲቀይሩ ምክንያት እንደሆኗቸው ይገልጻሉ። ከአርሶ አደር ወልዴ በወሰዱት ልምድ ወደ ጥምር ግብርና ገብተዋል። በዚህም ድርቅ የመቋቋም አቅም ያለውን እንሰት በማሳቸው በስፋት ማልማት ጀምረዋል። የነበሯቸውን ሀገረሰብ የዳልጋ ከብቶች በተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች በመቀየር የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ተግተው እየሰሩ ነው። ጥምር ግብርና የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ከአርሶ አደር ወልዴ ተምሪያለሁ ይላሉ። ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባለፈ የመሬት ለምነትን ለማስጠበቅም ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ የጀመርነውን ሥራ እናጠናክራለን ሲሉም ነው የገለጹት። የሙህር አክሊል ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ መኑር ጀማል በበኩላቸው "አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ በውስን መሬት ገብስ፣ እንሰት፣ ቡና እና የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በጥምር በማልማት የራሳቸውን ህይወት ከመቀየር ባለፈ ለሌሎች አርሶ አደሮች አርአያ እየሆኑን ነው ብለዋል። አርሶ አደሩ በሽታ መቋቋም የሚችሉና ለመድሃኒትነት የሚፈለጉ የእንሰት ዝርያዎችን በማፍላት ለገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ። ከዚህም ባለፈ በመጥፋት ላይ የነበሩ የእንሰት ዝርያዎችን የመታደግና የአፈር ለምነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውንም ተናግረዋል፡፡ የጥምር ግብርና አሰራር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ በመሆኑ በወረዳው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት። የአርሶ አደር ወልዴ ልምድን በማስፋት የሌሎች አርሶ አደሮችም ጓዳ ሞልቶ እንዲትረፈረፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጥምር ግብርና አርሶ አደሩ ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ጭምር እንዲተርፍ የማድርጉ ሥራ ይጠናከራል ብለዋል። ልማቱ እርስ በእርስ የሚደጋገፉና በአንድ መሬት ላይ የተለያዩ ምርቶችን በማግኘት የተሻለ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚሰራው ሥራ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ በጥቂት መሬት ብዙ ማምረት መቻል ነው። በመሆኑም በተለይ የመሬት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በሥራ ውጤታማ ለመሆን ሁሉም ነገር ምቹና አልጋ በአልጋ መሆን የግድ እንዳልሆነ አርሶ አደሩ ጥሩ ማሳያ ናቸው። ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ዕድል እንዴት ወደሀብትነት መቀየር እችላለሁ ብለው ከሰሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ የእሳቸው የስኬት ጉዞ በቂ ማሳያ ነው። ሰርቶ ለመለወጥም ሆነ ሀብት ለማፍራት ችግሮችን በጽናት ማለፍ እና የሥራ ትጋት ወሳኝ ነውና ተሞክሯቸውን ማስፋት ያስፈልጋል።
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ"
Nov 12, 2025 363
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ" ብርሃኑ ፍቃዱ -ከሰቆጣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልካዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረት ያለው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ማብራራታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ የባህር በሯን ያጣችበትን የ30 ዓመታት ታሪክ ለመቀልበስ ይህን ያህል ዓመት እንደማይወስድ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ ሕጋዊና ተቋማዊ መሰረት የሌለው የሚያስቆጭ ብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል ስለመሆኑም አንስተዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ እና አቶ አድማሱ ደሳለኝ፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር የተወለዱበት ስፍራ፣ የኖሩበት ቀዬ፣ ያሳደጋቸው ማህበረሰብ ... የዘመናት ትዝታና ትውስታቸው እንደሆነ ይገልጻሉ። ይህን የታሪካቸው አካል የሆነውን የባሕር በር ማጣትም የሁል ጊዜ ፀፀትና እንደ ሰውነት ጥላ አብሮዋቸው የሚዞር እውነታ ነው። ከአካባቢው ርቆ ለሚገኝ ሰው ትውስታውን ሲያወራ ለሌላው ተረት ተረት፤ ለራስ ደግሞ የውስጥ ቁስል ማገርሸት ሆኖ ነው የሚሰማው ይላሉ። ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብንና የቀይ ባህር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሸፍጥ ማጣቷ በቀይ ባህር ላይ እየዋኙ፣ ውሃ እየተራጩ፣ በዳርቻው ነፋሻማ ስፍራ እየተዝናኑ... ለኖሩት ለእነ መለሰ እና አድማሱ መቼም የማይረሳ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ለአለም ማሕበረሰብ ጥያቄውን ሲያሳውቁ ተደብቆ ለቆየው ትውስታቸው አዲስ ተስፋ እንደሰጣቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ በአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል ለ12 ዓመታት እንዳገለገሉ በትውስታና ቁጭታቸውን ወደ ኋላ ተመልሰው ያወሳሉ። አሁን በሰቆጣ ከተማ የሚኖሩት አቶ መለሰ ይሄይስ ፤ የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ተደማሪ አቅም ነበር በወቅቱ ይላሉ። ይህን የአሰብ ወደብንና የቀይ ባሕር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሴራ ኢትዮጵያ ስታጣ ይሰሩበት ከነበረው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ስራ አቁመው ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሰቆጣ መምጣታቸውን አውስተዋል። በራሳቸው ላይ ከደረሰባቸው የስራ እና ሃብትና ንብረት ማጣት ፣ እንግልትና ሌሎች ችግሮች በላይ ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተነጠለችበትን ሁኔታ ሲያስቡና ሲያሰላስሉ እንደሚያስቆጫቸው ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን በማጣት የባሕር በር ብቻ ሳይሆን የገቢና ወጭ ንግድን፣ የነዳጅ ማጣሪያ ጭምር ነው ያጣችው ያሉት አቶ መለሰ፤ አሁን ጥያቄው መነሳቱ ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ ገናናነቷ ለመመለስ ያለመ አበረታች ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። መንግስት ያነሳው የባሕር በር ጥያቄም የዘመናት ቁጭታችንን፣ ብስጭታችንን እና ህልማችንን ከተደበቀ ትውስታ፤ ወደ አዲስ ተስፋ የወሰደ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ህጋዊና ታሪካዊ ነው ያሉት አቶ መለሰ ፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝም ለአዲሱ ትውልድ በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። ከ1973 ዓ.ም ጀምረው ለአስር ተከታታይ ዓመታት በአሰብ ወደብ የሲቪል መሃንዲስ ክፍል ሰራተኛ እንደነበሩ ያወሱት አቶ አድማሱ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የባሕር ባር ባለቤት በሆነችባቸው ዘመናት ገናና እና የተከበረች ሀገር ሆና መቆየቷን አንስተዋል። የባሕር በሩ የኢትዮጵያ የገቢና ወጭ ንግድ የሚሳለጥበት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሄን ታላቅ ትሩፋትና ፀጋ ለማስመለስ የተጀመረው እንቅስቃሴ ቁጭትና ትውስታችንን ወደ አዲስ ተስፋ የቀየረ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪካዊ ጠላቶችና ባንዳዎች እኩይ ሴራ የባሕር በር ካጣች ወዲህ ጥያቄውን ማንሳት የማይቻልበት የአፈናው ዘመን አክትሞ በለውጡ መንግስት መነሳቱ አበረታችና ለማስመለስም ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። እኔም ባለኝ አቅም ሁሉ ስለባሕር ባር አስፈላጊነት፣ ጥቅምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ለስኬታማነቱ የድርሻዬ እወጣለሁ ሲሉም ገልጸዋል።