ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ክፍያ አማራጭ ለደንበኞቹ ምቹ አገልግሎት እየሰጠ ነው
Oct 30, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 2ዐ/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎች ክፍያ አማራጭ ለደንበኞቹ ምቹ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሆሊደይ፣ዲጅታል ሽያጭ እና ዓለም አቀፍ የደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ምክትል ፕሬዝዳንት ኃይለመለኮት ማሞ ገለጹ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኦንላይን የክፍያ አማራጭ ስርዓት አቅራቢ ከሆነው ቻፓ ካምባኒ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል። የመግባቢያ ሰነዱን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሆሊደይ፣ ዲጅታል ሸያጭ እና ዓለም አቀፍ የደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ምክትል ፕሬዝዳንት ኃይለመለኮት ማሞ እና የቻፓ ካምፓኒ መስራችና ስራ አስኪያጅ ናኤል ሃይለማሪያም ፈርመዋል። አቶ ኃይለመለኮት ማሞ በዚሁ ወቅት፤ አየር መንገዱ የደንበኞችን አገልግሎት ለማዘመን በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡ በዚህም በተለይ የአሰራር ስርዓቱን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በርካታ ለውጦችን አስመዝግበዋል ነው ያሉት፡፡ በዛሬው እለት ሀገር በቀል ቴክኖሎጂ ከሆነው ቻፓ ካምፓኒ ጋር የተደረገው ስምምነት የሀገር ውስጥና የውጭ ደንበኞችን የኦንላይን የክፍያ ስርዓት ይበልጥ ምቹ እና ቀልጣፋ የሚያደርግ ነው ብለዋል። ደንበኞች ሞባይል ባንኪንግን፣ቴሌ ብርንና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የበረራ ትኬቶቻቸውን በኦንላይን እንዲቆርጡ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎች ደህንነቱ የተጠበቀ ክፍያን ለመፈጸም ሁነኛ አማራጭ በመሆናቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እነዚህን ቴክኖሎጂዎች መጠቀሙን አጠናክሮ ይቀጥል፤ድጋፍም ያደርጋል ነው ያሉት። የቻፓ ካምፓኒ መስራችና ስራ አስኪያጅ ናኤል ሃይለማሪያም በበኩላቸው፤ ቴክኖሎጂው በኢትዮጵያ ውስጥ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ለአጠቃቀም ምቹ የሆነ የኦንላይን ክፍያ የሚሰጥ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ነው ብለዋል፡፡ ቴክኖሎጂው በኢትዮጵያ ውስጥ የኢ-ኮሜርስ ንግድ እንዲስፋፋ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል፡፡ ዓለም አቀፍ እና ከሀገር ውስጥ ደንበኞች ኦንላይን ክፍያዎችን መፈጸም እንደሚያስችል ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ምድቡን መቀላቀል ሳይችል ቀርቷል
Oct 30, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ሁለተኛ ዙር ከወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒራሚድስ ጋር ዛሬ ባደረገው የመልስ ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፏል። ማምሻውን በጁን 30 ኤር ዲፌንስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሙስጠፋ ዚኮ እና ኤወርተን ዳ ሲልቫ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳረፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ፒራሚድስ በድምር ውጤት 3 ለ 1 በማሸነፍ ምድብ ድልድሉን መቀላቀል ችሏል። ክለቦቹ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ አንድ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ መድን የመጀመሪያ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው ሁለተኛ ዙር ላይ ተገቷል። ቡድኑ አምናው በታሪኩ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ማሸነፉን ተከትሎ ነው በአህጉራዊ መድረክ የመሳተፍ እድል ያገኘው። የግብጹ ፒራሚድስ ክለብ የወቅቱ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ የዋንጫ ባለቤት ነው።
የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብት ምርታማነት ለማዘመን የተተገበሩ ቴክኖሎጂዎች የዜጎችን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ነው
Oct 30, 2025 65
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብት ምርታማነት ለማዘመን የተተገበሩ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የዜጎችን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። ከዛሬ ጥቅምት 20 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሶስት ቀናት የሚቆይ የእንስሳት ሃብት ልማት፣ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን የሚያሳይ አውደ ርዕይና ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በአውደ ርዕይና ጉባኤው የተለያዩ ሀገራትን የወከሉ የግብርና ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የእንስሳት ሃብት ልማትና ተዋፅኦ ምርቶች፣ የዓሳና ንብ ማነብ ስራዎችን ለዕይታ ቀርበዋል። በዚሁ ወቅት በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አለማየሁ መኮንን (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብት ለማዘመን የተተገበሩ ቴክኖሎጂዎች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው። የሌማት ትሩፋትን ጨምሮ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ተግባራዊ የተደረጉ የእንስሳት ሃብት ልማት ስራዎች የዜጎችን ተጠቃሚነት እያሳደጉ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ለአብነትም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ከፍተኛ የእንስሳት ሃብት ምርታማነት የማሳደግ የዝርያ ማሻሻል ስራ በዜጎች ህይወት ላይ እመርታዊ ለውጥ ለማስመዝገብ ማስቻሉን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የኔዘርላንድስ አምባሳደር ክርስቲን ፕረን፤ የኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነት መርሃ ግብሮች የሀገሪቷን ዕድገት እየደገፉ ነው ብለዋል። የኔዘርላንድስ መንግስትም የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብትና የግብርና ምርታማነት ልማት የእሴት ሰንሰለት ለማሻሻል ለሚከናወኑ ጥረቶች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የፕራና ኢቨንትስ ማኔጅንግ ዳይሬክተር ነብዩ ለማ፤ አውደ ርዕዩ የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብት ምርታማነት የሚያሻሽል የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የግብዓት አቅርቦትና የገበያ ትስስርን መፍጠር ያስችላል ብለዋል። የአውደ ርዕዩ ተሳታፊ የሆኑት ዮዲት ቤተ-ማርያም፤ አውደ-ርዕዩ የወተት ማቀነባበሪያ ማሽነሪ ምርቶቻቸውን ለአርሶ አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ የገበያ ትስስርን ለመፍጠር ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው ገልጸዋል። ሌላኛው የአውደ ርዕዩ ተሳታፊ ማዕረግ ገብረ-እግዚአብሔር፤ አውደ ርዕዩ የማር ምርታቸውን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት መድረክ ነው ብለዋል። ከቻይና መጥተው የእንስሳት መኖ ማቀነባባሪያ ቴክኖሎጂን በአውደ ርዕዩ ያቀረቡት ዴቪን ሊዩ፤ ምርታቸውን ለኢትዮጵያና ተሳታፊ ሀገራት እያስተዋወቁ እንደሚገኙ ገልጸዋል። አውደ ርዕዩ የዶሮ ምርታማነትን የሚሻሽሉ ቴክኖሎጂዎችን በኢትዮጵያ ገበያ ለማቅረብ ዕድል ፈጥሮልናል ያሉት ደግሞ ከቱርክዬ በመምጣት የዶሮ ቤት በአውደ ርዕዩ ያቀረቡት ፉርከን ኤልማሊ ናቸው።
የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል የአካባቢውን አርሶ አደሮች ይበልጥ ውጤታማ እያደረገ ነው
Oct 30, 2025 66
ወራቤ ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ):- የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል የተሻሻሉ ዝርያዎችን በማቅረብ እና በሙያ ያደረገላቸው ድጋፍ የግብርና ልማታቸውን ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን እያገዛቸው መሆኑን በስልጤ ዞን የአሊቾ ውሪሮ ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል በዘር ብዜት፣ በምርምርና በቴክኖሎጂ ሽግግር የምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም ድጋፍ የተከናወኑ ሥራዎች በስልጤ ዞን አሊቾ ውሪሮ ወረዳ በመስክ ተጎብኝቷል፡፡ በዚህ ወቅት በወረዳው የሽልማት ቀበሌ አርሶ አደር ነስራ ከማል በሰጡት አስተያየት፤ ከዚህ ቀደም የግብርና ሥራቸውን በባህላዊ መንገድ ስለሚያከናውኑ በልፋታቸው ልክ ውጤታማ ሳይሆኑ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በምርምር ማዕከሉ የሚቀርበውን የሰብል ምርጥ ዘርና ሌሎች የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን በባለሙያዎች ታግዘው በመተግበር ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱንም ተናግረዋል፡፡ በዚህም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እየተሻሻለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ማዕከሉ በሰብል ዝርያና በሙያ በሚያደርግላቸው ድጋፍ ውጤታማነታቸው እያደገ መምጣቱን የተናገሩት ሌላው አርሶ አደር ናሲያ ጃቢር ናቸው፡፡ በተለይ በመስመር መዝራትን ጨምሮ ሌሎች የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን ተጠቅመው ከሚያለሙት ገብስ፣ ስንዴና አተር የተሻለ ምርት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዝርያዎቹ ፈጥነው ከመድረስ ባለፈ በምርት ይዘታቸው ከፍተኛና በሽታ መቋቋም የሚችሉ ናቸው ያሉት አርሶ አደሩ፤ በመሥመር መዝራቱም በተለምዶ በብተና ከሚደረገው አዘራር በተሻለ ውጤታማ እንዲሆኑ ያገዛቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደሥላሴ በወቅቱ እንዳሉት፤ የምርምር ማዕከሉ በክልሉ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያገዘ ነው፡፡ በዚህም በሌማት ትሩፋትና በአካባቢ ጥበቃ ሥራው ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ስለመሆኑ አንስተዋል፡፡ በምርምር ማዕከሉ እገዛ እየተገኙ ያሉ ስኬቶችን የማስፋት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ጉብኝቱ የምርምር ማዕከሉ ግብርናውን ለማዘመን የሚያከናውናቸው ሥራዎችን ለባለድርሻ አካላት የማሳወቅ፣ ግብዓት የማግኘትና ተሞክሮ መለዋወጥን ዓላማ ያደረገ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ያዕቆብ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ ማዕከሉ የስንዴ፣ ገብስ፣ ቦሎቄ፣ ተልባ፣ እንሰትና የእንስሳት ዝርያን ማሻሻል ጨምሮ ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነት ለማሻሻል የሚያግዙ ተግባራት ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በጉብኝቱ ላይ የክልሉ ግብርና፣ ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ አመራሮች እና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል፡፡
በሊጉ ድሬዳዋ ከተማ ሲያሸንፍ አዳማ ከተማ ከሀዲያ ሆሳዕና አቻ ተለያይተዋል
Oct 30, 2025 66
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ተካሄደዋል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታን 2 ለ 1 አሸንፏል። አሰጋኸኝ ጴጥሮስ በ31ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ግብ መቀሌ 70 እንደርታ መሪ ሆኗል። መሐመድ ኑር ናስር በ49ኛው እና አቤል አሰበ በ93ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፏቸው ጎሎች ድሬዳዋ ከተማን አሸናፊ አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ በስድስት ነጥብ ደረጃውን ወደ ሰባተኛ ከፍ አድርጓል። መቀሌ 70 እንደርታ በአንድ ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል። በተያያዘም አዳማ ከተማ ከሀዲያ ሆሳዕና በአዲስ አበባ ስታዲየም ያደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አዳማ ከተማ በሶስት ነጥብ 11ኛ፣ ሀዲያ ሆሳዕና በሁለት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የሶስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የአራተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳል።
ፖለቲካ
ሰላምን በማጽናት ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እየተወጣን ነው
Oct 30, 2025 105
ደሴ/ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡-ሰላምን በማጽናት ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን የደሴ እና የደብረ ብርሃን ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ገለጹ። የደሴ ከተማ አስተዳደር "ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ዛሬ የውይይት መድረክ አካሂዷል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ወይዘሮ ሄለን አሰፋ እንደገለጹት፣ የከተማዋን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ከመንግስት ጎን በመሰለፍ የድርሻቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በደሴ ከተማ ሰላም መስፈኑ የንግድ ሥራቸውን ያለምንም ችግር ለማከናወንና ቤተሰባቸውን ለመምራት እንዳስቻላቸውም ገልጸዋል። የከተማዋን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ሂደት በንቃት ከመሳተፈ ባለፈ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል የከተማዋ ልማት እንዲፋጠን የድርሻቸውን መወጣታቸውን አስረድተዋል። ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ አህመድ ጀማል በበኩላቸው ለጤናማ የንግድ እንቅስቃሴ የሰላም ዋጋ የማይተካ ነው ብለዋል። አሁን ላይ በአካባቢው ሰላም በመስፈኑ ምርትና ሸቀጣሸቀጥ ከሌላ አካባቢ ወደ ከተማዋ በማምጣት ሥራቸውን በአግባቡ ለማከናወን መቻላቸውን ተናግረዋል። በአካባቢያቸው የሰፈነውን ሰላም በመጠበቅ የንግድ ሥራቸውንና ልማትን ለማፋጠን ቁርጠኛ መሆናቸውን የገለጹት አቶ አህመድ፣ የታጠቁ ኃይሎችም የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ህብረተሰቡን መካስ እንዳለባቸው ተናግረዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ ካሳው በበኩላቸው የንግዱ ማህበረሰብ የደሴ ከተማና አካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ከመንግስት ጋር በትብብር የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል። ወጣቶችን ስለ ሰላም ከማስተማር በተጨማሪ ገበያው እንዲረጋጋ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ ዜና በደብረ ብርሀን ከተማ የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት የከተማቸውን ሰላም በማጠናከር ልማት እንዲፋጠን ከመንግስት ጎን ሆነው የሚያደርጉትን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። የከተማዋ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት በዘላቂ ሰላምና በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ከከተማው መስተዳድር ኃላፊዎች ጋር ዛሬ መክረዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ንጉሴ ማሞ ሰላም ለሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ለከተማቸው ሰላም መጠናከር የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። የንግድ ስራቸውን ለማከናወንም ሆነ ከልማት ሥራዎች ተጠቃሚ ለመሆን ሰላም ወሳኝ መሆኑን እና በከተማቸው የሰፈነውን ሰላም ለማስቀጠል የህዝብ ትብብር አስፈላጊ ነው ብለዋል። የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻልና የልማት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ሰላምን ማጽናት አይነተኛ ሚና እንዳለው የገለጹት ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ ደግሞ አቶ ሳሙኤል አውግቸው ናቸው። የሰላም እጦት ያለውን ተጽዕኖ እናውቀዋለን ያሉት ነዋሪው፣ ለሸቀጦች ዋጋ መናርና መጥፋት አንድ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል። የንግድ ሥራቸውን በተረጋጋ ሁኔታ ለማከናወንና ሁለንተናዊ ልማት እንዲፋጠን በከተማቸው የሰፈነውን ሰላም ለማጽናት ተግተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ለእዚህም እንደ ንግዱ ማህበረሰብ አባል ከመንግስት ጎን በመቆም የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። በተለይ ስለሰላም አስፈላጊነትና ሰርቶ ለመለወጥ ሰላም ያለውን ፋይዳ ለህብረተሰቡ የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። መንግስት የጀመራቸው የልማት ስራዎች ዳር እንዲደርሱና በሰላም ወጥቶ ለመግባት ዘላቂ ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላማቸው ቁርጠኛ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ሼህ ኡስማን መሐመድ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ደመረ ላቀው በበኩላቸው እንደገለጹት የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ከመንግስት ጎን ሆነው ለሰላም ያሳዩት ተነሳሽነት የሚበረታታ ነው። የዛሬው መድረክም የሰላም እጦት በኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለማስገንዘብ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። ነጋዴው ሰርቶ ተጠቃሚ መሆን የሚችለው ሰላም በዘላቂነት ሲረጋገጥ መሆኑን ጠቅሰው፣ ህብረተሰቡ ለአካባቢው ሰላም መጠናከር ከመንግስት ጎን በመሆን የጀመረውን ተግባር እንዲያጠናክር አሳስበዋል። በደሴ እና በደብረብርሀን ከተሞች በተካሄዱ የውይይት መድረኮች የንግዱ ማህበረሰብ፣ አመራሩና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ አቋማችን የማይናወጥ ነው -የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Oct 30, 2025 173
ሚዛን አማን ፤ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ)፡-የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖረንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ ግን አቋማችን የማይናወጥና አንድ ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ። በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ እየጎለበተ እንዲሄድ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። በዚህም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፌዴራልና በክልሎች የጋራ ምክር ቤት በመመስረት የሀሳብ ክርክሮችን በማድረግ በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ እየሰሩ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ የሀገር ልማትና የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ዙሪያ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ኢዜአ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን አነጋግሯል። የፓርቲዎቹ አመራሮችም የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ ግን አቋማችን አንድና ሊናወጥ የማይችል ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት የሚያስቆጭና መልሳ ማግኘት እንዳለባት የጸና እምነት እንዳላቸው አንስተው በዚህ ረገድ መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴና ያለውን አቋም እናደንቃለን ብለዋል። የባህር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ የህልውና ጉዳይ ተደርጎ መያዙ ሁላችንንም የሚያስማማ በመሆኑ በሁሉም ረገድ የመንግስትን አቋም እንደግፋለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ፓርቲ ተወካይ ጎዳና ሙንኤ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ምክንያቱ የማይታወቅ፣ የሁልጊዜም ቁጭትና የታሪክ ስብራት ጭምር መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና መንግስታቸው የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን በፅኑ አምኖ ምላሽ እንዲያገኝ የጀመረውን ጥረት እናደንቃለን፤ እንደግፋለንም ብለዋል። የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ በሉአላዊነቷ እና በተለይም በባህር በር ጉዳይ ላይ አቋማችን ሊናወጥ አይችልም ሲሉም አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባልና ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አቶ ሰሎሞን መኮንን፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት ብሔራዊ ጥቅሟን በእጅጉ የጎዳ፣ የሚያስቆጭና የታሪክ ተወቃሽ የሚያደርግ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም ምክንያት እስካሁን ኢትዮጵያ ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለች መሆኑን ተናግረው መንግስት የባህር በር ሊኖራት የግድ ይላል ብሎ አቋም መያዙ ተገቢና ሁላችንም የምንደግፈው አጀንዳ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት በፍፁም የቀባይነት የሌለው መሆኑን አስታውሰው ከቀይ ባህር በቅርብ እርቀት ላይ ሆና የተቆለፈባት ሀገር ሆና መዝለቅ የለባትም ሲሉ አፅኖት ሰጥተዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በታሪክም፣ በህግም ይሁን በመልካአ ምድር የባህር በር የማግኘት መብት አላት ለዚህም ስኬት በጋራ እንቆማለን ሲሉ አረጋግጠዋል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን የሰፈነው ሰላም የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነታችንን እያሳደገ ነው - የዞኑ ነዋሪዎች
Oct 30, 2025 91
ጊምቢ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን የሰፈነው ሰላም የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የዞኑ ነዋሪዎች ገለጹ። በአካባቢው የሰፈነው ሰላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች በተሻለ መልኩ እንዲከናወኑ ማድረጉንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ የዞኑ ነዋሪዎች መካከል አቶ አያና መንገሻ ቀደም ሲል በአካባቢያችው አጋጥሞ የነበረው የጸጥታ ችግር ተወግዶ ሰላም በመስፈኑ በልማት ስራቸው ላይ እንዲተጉ አድርጓቸዋል፡፡ ይህም ክረምት ከበጋ በልማት ስራዎች ላይ የሚያደርጉት ተሳትፎ እንዲጎለብትና ተጠቃሚነታቸው እያደገ እንዲመጣ ማድረጉን ተናግረዋል። በተለይም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው የልማት ስራዎቹ ለስኬት እንዲበቁና የተገኘው ሰላም ቀጣይ እንዲሆን የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም ገልጸዋል። በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ በአካባቢያቸው በሰፈነው ሰላም ያለ ስጋት ተንቀሳቅሰው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስራዎቻቸውን ማከናወናቸውን የሚናገሩት ደግሞ ወይዘሮ አያንቱ ሆራ ናቸው፡፡ በቀጣይም የልማት ስራዎች እንዲቀጥሉ ሰላምን ለማጽናት በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩ አውስተዋል። አቶ መገርሳ አጋ የተባሉት ነዋሪ በበኩላቸው በዞኑ በሰፈነው ሰላም በሁሉም መስክ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የተሟላ መሆኑንና በተለይም አርሶ አደሩ ያለምንም ስጋት የእለት ተዕለት ስራውን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ሰላምን ዘላቂ ከማድረግ አንጻር ከአካባቢያቸው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር በልማት ስራ ላይ እያደረጉት ያለውን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል። የምዕራብ ወለጋ ዞን ጸጥታ እና አስተዳዳር ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ጌታሁን ተርፋሳ እንደገለጹት በዞኑ ህዝቡ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር ተባብሮ በመስራቱ ዘላቂ ሰላም ሰፍኗል። ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት ተንቀሳቅሶ ተግባሩን እንዲያከናውን ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ በሙሉ ልቡ የልማት ስራ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል ብለዋል። በሰፈነው ሰላምም የተጀመሩ የልማት ስራዎች መቀጠላቸውንና የተገኘውን ሰላም አጽንቶ ለማቆየት ህዝቡ ሚናውን ማጠናከር ይገባል ነው ያሉት።
የብልፅግና ፓርቲ ዓመታዊ ስልጠና ማካሄድ ጀመረ
Oct 30, 2025 142
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡- የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ማካሄድ ጀምሯል። ስልጠናው "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሐሳብ ለሚቀጥሉት 10 ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ይሆናል። ስልጠናው የአመራሩን ዕውቀት፣ ክኅሎትና ዐቅም የሚገነቡ ልዩ ልዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚቀርቡበት መሆኑም ተገልጿል። በስልጠናው ከ2ሺህ በላይ ከፌዴራልና ከክልል የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች እንደሚሳተፉ ተጠቁሟል። ከስልጠናው በተጓዳኝ የተግባር የመስክ የልማት ሥራ ጉብኝቶች እንደሚካሄድም ተመላክቷል።
በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን ለማጽናትና ልማትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን
Oct 29, 2025 181
ደብረ ብርሃን/ ገንዳ ውሃ/ደሴ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፡ - በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን ለማጽናትና ልማትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተናገሩ። በአማራ ክልል በደብረ ብርሃን፣ ገንዳ ውሃ እና ደሴ ከተሞች የሚገኙ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። ከደብረ ብርሃን ከተማ የውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ቀሲስ እሸቱ ተክለዮሃንስ እና አቶ ሁሴን ይመር፤ በከተማዋ አሁን ላለው ሰላምና ልማት የነዋሪውና የጸጥታ ሃይሉ የተቀናጀ ጥረት ውጤት መሆኑን አንስተዋል። የሰላም ጉዳይ ለማንም የማንተወው የጋራ አጅንዳችን ሆኖ ቀጥሏል ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ሰላምን ለማጽናትና ልማትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የከተማዋ የሀገር ሽማግሌ የሆኑት አቶ ለገሰ ሽፈራው፣ በበኩላቸው የሰላም ጥረታችን እና የልማት ትጋታችን ወደ ኋላ የማይመለስ ነው ብለዋል። በመሆኑም ለከተማዋና አካባቢው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥና ለተጀመሩ የልማት ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው በተለይም የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶችና አጠቃላይ ማህበረሰቡ ጠንካራ ተሳትፎና ትብብር በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳንኤል እሸቴ፤ ለማንኛውም ችግር መፍትሄዊ ሰላማዊ ውይይት መሆኑን በማመን መንግስት በዚህ ረገድ ብዙ እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ጥረት ውስጥ በተለይም የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው የሰላም ጥረቶችንና የልማት አቅሞችን መጠቀማችን ቀጣይነት ይኖረዋል ብለዋል። በተያያዘ ዜና በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ የሃይማኖት አባት መላዕከ ኃይል ፍሬው ዘመነ፤ በበኩላቸው የአካባቢያቸውን ሰላም በማስፈን የተጀመረው ልማት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከመቼውም ግዜ በላይ ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ሌላኛው የመድረኩ ተሳታፊ የሀይማኖት አባትና የሀገር ሽማግሌ ሼህ አደም ሱሌማን፤ የሀገሪቱን እድገት የማይፈልጉ የውጭ ጠላቶች እና የውስጥ ባንዳዎች ሰላምን ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ እየጣሩ ስለመሆኑ እንገነዘባለን ብለዋል። በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች ለሰላማችን መረጋገጥና እና ለልማታችን ቀጣይነት በጋራ ቆመን መስራት ይገባናል ሲሉ አስገንዝበዋል። በደሴ ከተማ በተካሄደው ተመሳሳይ መድረክ ላይ የተገኙት መላከ ብርሃን ቆሞስ አባ ተስፋሚካኤል፣ ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ለሰላም ግንባታ የምንሰስተው ነገር ሊኖር አይገባም ብለዋል። ከግጭትና ጦርነት ጉዳት እንጅ ጥቅም አለመኖሩን በተግባር አይተናል ያሉት አባ ተስፋሚካኤል ሰላማችንን በመጠበቅ የተጀመሩ ሰፋፊ የልማት ስራዎችን ከዳር ማድረስ ይጠበቅብናል ሲሉ አስገንዝበዋል። ሌላኛው የሐይማኖት አባት ሼህ ሀሽም መሀመድ፣ ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላም መስፈን ከመንግስት ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ ካሳው፤ የከተማውን ሰላም ከሕብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር አስተማማኝ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በከተሞቹ በተካሄደው ውይይት ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
መንግስት በተደጋጋሚ የሚያቀርበው የሰላም አማራጭ ለዘላቂ ሰላምና እድገት መረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው
Oct 29, 2025 192
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት በተደጋጋሚ የሚያቀርበው የሰላም አማራጭ የሚደነቅና ለዘላቂ ሰላምና እድገት መረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ጥያቄ አለን የሚሉ ቡድኖች በመንግስት የቀረበውን የሰላም አማራጭ በመቀበል ልዩነታቸውን በውይይት ለመፍታት መዘጋጀት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ትናንት መካሄዱ ይታወቃል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። መንግሥት ወደ ሰላም ከሚመጣ የትኛውም ኃይል ጋር አብሮ ለመስራት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በድጋሚ አረጋግጠዋል። በዚህም የሰላምና የጸጥታ ችግር ለሚስተዋልባቸው አንዳንድ አካባቢዎች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት መንግሥት ለሰላም አማራጭ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የምክር ቤቱ አባላት ላነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ መንግስት ሰላምን ለማጽናት ያለውን ቁርጠኝነት ተገንዝበናል ብለዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ፈቃዱ ጳውሎስ፤ ሰላም የሀገርን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማስቀጠል ሁነኛ መሳሪያ መሆኑን ገልጸዋል። ከሰላማዊ አማራጭ ውጪ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የሀገርን ልማትና ዕድገት በማደናቀፍ ዜጎችን ለእንግልት የሚዳርጉ መሆናቸውንም አንስተዋል። በዚህም የመንግስትን የሰላም ጥሪ ያልተቀበሉ ቡድኖች የሰላም አማራጭን በመቀበል አሉኝ የሚሏቸውን ጥያቄዎች በሰለጠነ መንገድ በውይይት መፍታት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። የሰላምን መንገድ በመምረጥ ህዝብና ሀገራቸውን በመካስ የሀገር ዕድገት አቅም እንዲሆኑም ነው የተናገሩት። በቀጣይም ለሀገር ሰላምና አንድነት በጋራ በመቆም የኢትዮጵያን ከፍታና የህዝብን ተጠቃሚነት በሚያስቀጥሉ የልማት ዘርፎች በትብብር መስራት አለብን ብለዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ሀቢብ አህመድ፤ ሰላም ለዜጎች ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ መሰረት መሆኑን ጠቅሰው ሁሉም ዜጋ የሰላም አርበኛ በመሆን ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት በጋራ መቆም እንዳለበት ገልጸዋል። ሀገራዊ የሰላም ግንባታ የሁሉንም ዜጋ ቀና ትብብር የሚጠይቅ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አያሌው ዘለቀ ጠቅሰዋል። ወይዘሮ ሸዋንብረት ማሞ በበኩላቸው፤ የሰላም አማራጭን ያልተከተሉ ወገኖች ምክክርን ሊያስቀድሙ ይገባል ብለዋል። የመንግስት የሰላም አማራጭ የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት ያስችላል ያሉት ወይዘሮ ሸዋንብረት፤ በጫካ የሚንቀሳቀሱ ወገኖችም የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ መክረዋል።
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)
Oct 29, 2025 223
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር በመሰረተ ልማት ያላትን ትስስር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላትም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በደቡብ ሱዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስቴር ፒዬንግ ዴንግ ኩኦል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ልዑካን ቡድኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን በተለይም በአቢዬ ግዛት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ገለጻ አድርጓል። ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አጠናቃ በስኬት በማስመረቋ ደስታቸውን በመግለጽ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት በህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ በመሳተፋቸውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በመሰረተ ልማት የበለጠ በመተሳሰር ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጎልበት ሊሰሩ እንደሚገባም መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ የሚገባትን የባሕር በር መጠየቋ ቅንጦት አይደለም - ምሁራን
Oct 29, 2025 191
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ መልማቷን ባልፈለጉ አካላትና ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በትላንትናው እለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቀይ ባሕር ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባሕር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ-ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን ኢትዮጵያ ታምናለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ የወሰነው ማን ነው ብለን ስንፈትሽ ማስረጃ አልተገኘም፤ ተቋማትም እንዳልገቡበት አንስተዋል። ባሕር በር የኅልውና ጉዳይ በመሆኑ ኢትዮጵያም ተዘግቶባት መኖር ስለማትችል ጥረቷ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን በጉዳዩ ላይ እንዳሉት ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን ባልፈለጉ አካላት በተንኮል የተነጠቀችውን የአካሏን ክፋይ መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ አስረድተዋል። የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ፤ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን ያጣችበት ሂደት ግፍ እንጂ ሕጋዊ አለመሆኑን አንስተው፤ መንግሥት ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት አምኖ አጀንዳ ማድረጉ ከሕግም ሆነ ከሞራል አንጻር ትክክል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንድታጠናክርም መክረዋል። በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ ያሬድ አያሌው (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚ መሆን ፋይዳው የቀጣናውም ጭምር እንደሚሆን አስረድተዋል። ቀጣናውን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያ የጠየቀችው የአካሏን ክፋይና ህጋዊ መብት መሆኑን በመገንዘብ ለጋራ ተጠቃሚነት ሲሉ ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል።
ፖለቲካ
ሰላምን በማጽናት ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እየተወጣን ነው
Oct 30, 2025 105
ደሴ/ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡-ሰላምን በማጽናት ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን የደሴ እና የደብረ ብርሃን ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ገለጹ። የደሴ ከተማ አስተዳደር "ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ዛሬ የውይይት መድረክ አካሂዷል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ወይዘሮ ሄለን አሰፋ እንደገለጹት፣ የከተማዋን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ከመንግስት ጎን በመሰለፍ የድርሻቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በደሴ ከተማ ሰላም መስፈኑ የንግድ ሥራቸውን ያለምንም ችግር ለማከናወንና ቤተሰባቸውን ለመምራት እንዳስቻላቸውም ገልጸዋል። የከተማዋን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ሂደት በንቃት ከመሳተፈ ባለፈ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል የከተማዋ ልማት እንዲፋጠን የድርሻቸውን መወጣታቸውን አስረድተዋል። ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ አህመድ ጀማል በበኩላቸው ለጤናማ የንግድ እንቅስቃሴ የሰላም ዋጋ የማይተካ ነው ብለዋል። አሁን ላይ በአካባቢው ሰላም በመስፈኑ ምርትና ሸቀጣሸቀጥ ከሌላ አካባቢ ወደ ከተማዋ በማምጣት ሥራቸውን በአግባቡ ለማከናወን መቻላቸውን ተናግረዋል። በአካባቢያቸው የሰፈነውን ሰላም በመጠበቅ የንግድ ሥራቸውንና ልማትን ለማፋጠን ቁርጠኛ መሆናቸውን የገለጹት አቶ አህመድ፣ የታጠቁ ኃይሎችም የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ህብረተሰቡን መካስ እንዳለባቸው ተናግረዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ ካሳው በበኩላቸው የንግዱ ማህበረሰብ የደሴ ከተማና አካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ከመንግስት ጋር በትብብር የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል። ወጣቶችን ስለ ሰላም ከማስተማር በተጨማሪ ገበያው እንዲረጋጋ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ ዜና በደብረ ብርሀን ከተማ የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት የከተማቸውን ሰላም በማጠናከር ልማት እንዲፋጠን ከመንግስት ጎን ሆነው የሚያደርጉትን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። የከተማዋ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት በዘላቂ ሰላምና በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ከከተማው መስተዳድር ኃላፊዎች ጋር ዛሬ መክረዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ንጉሴ ማሞ ሰላም ለሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ለከተማቸው ሰላም መጠናከር የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። የንግድ ስራቸውን ለማከናወንም ሆነ ከልማት ሥራዎች ተጠቃሚ ለመሆን ሰላም ወሳኝ መሆኑን እና በከተማቸው የሰፈነውን ሰላም ለማስቀጠል የህዝብ ትብብር አስፈላጊ ነው ብለዋል። የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻልና የልማት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ሰላምን ማጽናት አይነተኛ ሚና እንዳለው የገለጹት ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ ደግሞ አቶ ሳሙኤል አውግቸው ናቸው። የሰላም እጦት ያለውን ተጽዕኖ እናውቀዋለን ያሉት ነዋሪው፣ ለሸቀጦች ዋጋ መናርና መጥፋት አንድ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል። የንግድ ሥራቸውን በተረጋጋ ሁኔታ ለማከናወንና ሁለንተናዊ ልማት እንዲፋጠን በከተማቸው የሰፈነውን ሰላም ለማጽናት ተግተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ለእዚህም እንደ ንግዱ ማህበረሰብ አባል ከመንግስት ጎን በመቆም የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። በተለይ ስለሰላም አስፈላጊነትና ሰርቶ ለመለወጥ ሰላም ያለውን ፋይዳ ለህብረተሰቡ የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። መንግስት የጀመራቸው የልማት ስራዎች ዳር እንዲደርሱና በሰላም ወጥቶ ለመግባት ዘላቂ ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላማቸው ቁርጠኛ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ሼህ ኡስማን መሐመድ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ደመረ ላቀው በበኩላቸው እንደገለጹት የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ከመንግስት ጎን ሆነው ለሰላም ያሳዩት ተነሳሽነት የሚበረታታ ነው። የዛሬው መድረክም የሰላም እጦት በኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለማስገንዘብ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። ነጋዴው ሰርቶ ተጠቃሚ መሆን የሚችለው ሰላም በዘላቂነት ሲረጋገጥ መሆኑን ጠቅሰው፣ ህብረተሰቡ ለአካባቢው ሰላም መጠናከር ከመንግስት ጎን በመሆን የጀመረውን ተግባር እንዲያጠናክር አሳስበዋል። በደሴ እና በደብረብርሀን ከተሞች በተካሄዱ የውይይት መድረኮች የንግዱ ማህበረሰብ፣ አመራሩና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ አቋማችን የማይናወጥ ነው -የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Oct 30, 2025 173
ሚዛን አማን ፤ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ)፡-የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖረንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ ግን አቋማችን የማይናወጥና አንድ ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ። በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ እየጎለበተ እንዲሄድ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። በዚህም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፌዴራልና በክልሎች የጋራ ምክር ቤት በመመስረት የሀሳብ ክርክሮችን በማድረግ በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ እየሰሩ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ የሀገር ልማትና የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ዙሪያ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ኢዜአ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን አነጋግሯል። የፓርቲዎቹ አመራሮችም የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ ግን አቋማችን አንድና ሊናወጥ የማይችል ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት የሚያስቆጭና መልሳ ማግኘት እንዳለባት የጸና እምነት እንዳላቸው አንስተው በዚህ ረገድ መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴና ያለውን አቋም እናደንቃለን ብለዋል። የባህር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ የህልውና ጉዳይ ተደርጎ መያዙ ሁላችንንም የሚያስማማ በመሆኑ በሁሉም ረገድ የመንግስትን አቋም እንደግፋለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ፓርቲ ተወካይ ጎዳና ሙንኤ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ምክንያቱ የማይታወቅ፣ የሁልጊዜም ቁጭትና የታሪክ ስብራት ጭምር መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና መንግስታቸው የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን በፅኑ አምኖ ምላሽ እንዲያገኝ የጀመረውን ጥረት እናደንቃለን፤ እንደግፋለንም ብለዋል። የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ በሉአላዊነቷ እና በተለይም በባህር በር ጉዳይ ላይ አቋማችን ሊናወጥ አይችልም ሲሉም አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባልና ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አቶ ሰሎሞን መኮንን፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት ብሔራዊ ጥቅሟን በእጅጉ የጎዳ፣ የሚያስቆጭና የታሪክ ተወቃሽ የሚያደርግ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም ምክንያት እስካሁን ኢትዮጵያ ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለች መሆኑን ተናግረው መንግስት የባህር በር ሊኖራት የግድ ይላል ብሎ አቋም መያዙ ተገቢና ሁላችንም የምንደግፈው አጀንዳ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት በፍፁም የቀባይነት የሌለው መሆኑን አስታውሰው ከቀይ ባህር በቅርብ እርቀት ላይ ሆና የተቆለፈባት ሀገር ሆና መዝለቅ የለባትም ሲሉ አፅኖት ሰጥተዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በታሪክም፣ በህግም ይሁን በመልካአ ምድር የባህር በር የማግኘት መብት አላት ለዚህም ስኬት በጋራ እንቆማለን ሲሉ አረጋግጠዋል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን የሰፈነው ሰላም የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነታችንን እያሳደገ ነው - የዞኑ ነዋሪዎች
Oct 30, 2025 91
ጊምቢ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን የሰፈነው ሰላም የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የዞኑ ነዋሪዎች ገለጹ። በአካባቢው የሰፈነው ሰላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች በተሻለ መልኩ እንዲከናወኑ ማድረጉንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ የዞኑ ነዋሪዎች መካከል አቶ አያና መንገሻ ቀደም ሲል በአካባቢያችው አጋጥሞ የነበረው የጸጥታ ችግር ተወግዶ ሰላም በመስፈኑ በልማት ስራቸው ላይ እንዲተጉ አድርጓቸዋል፡፡ ይህም ክረምት ከበጋ በልማት ስራዎች ላይ የሚያደርጉት ተሳትፎ እንዲጎለብትና ተጠቃሚነታቸው እያደገ እንዲመጣ ማድረጉን ተናግረዋል። በተለይም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው የልማት ስራዎቹ ለስኬት እንዲበቁና የተገኘው ሰላም ቀጣይ እንዲሆን የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም ገልጸዋል። በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ በአካባቢያቸው በሰፈነው ሰላም ያለ ስጋት ተንቀሳቅሰው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስራዎቻቸውን ማከናወናቸውን የሚናገሩት ደግሞ ወይዘሮ አያንቱ ሆራ ናቸው፡፡ በቀጣይም የልማት ስራዎች እንዲቀጥሉ ሰላምን ለማጽናት በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩ አውስተዋል። አቶ መገርሳ አጋ የተባሉት ነዋሪ በበኩላቸው በዞኑ በሰፈነው ሰላም በሁሉም መስክ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የተሟላ መሆኑንና በተለይም አርሶ አደሩ ያለምንም ስጋት የእለት ተዕለት ስራውን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ሰላምን ዘላቂ ከማድረግ አንጻር ከአካባቢያቸው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር በልማት ስራ ላይ እያደረጉት ያለውን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል። የምዕራብ ወለጋ ዞን ጸጥታ እና አስተዳዳር ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ጌታሁን ተርፋሳ እንደገለጹት በዞኑ ህዝቡ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር ተባብሮ በመስራቱ ዘላቂ ሰላም ሰፍኗል። ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት ተንቀሳቅሶ ተግባሩን እንዲያከናውን ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ በሙሉ ልቡ የልማት ስራ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል ብለዋል። በሰፈነው ሰላምም የተጀመሩ የልማት ስራዎች መቀጠላቸውንና የተገኘውን ሰላም አጽንቶ ለማቆየት ህዝቡ ሚናውን ማጠናከር ይገባል ነው ያሉት።
የብልፅግና ፓርቲ ዓመታዊ ስልጠና ማካሄድ ጀመረ
Oct 30, 2025 142
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡- የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ማካሄድ ጀምሯል። ስልጠናው "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሐሳብ ለሚቀጥሉት 10 ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ይሆናል። ስልጠናው የአመራሩን ዕውቀት፣ ክኅሎትና ዐቅም የሚገነቡ ልዩ ልዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚቀርቡበት መሆኑም ተገልጿል። በስልጠናው ከ2ሺህ በላይ ከፌዴራልና ከክልል የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች እንደሚሳተፉ ተጠቁሟል። ከስልጠናው በተጓዳኝ የተግባር የመስክ የልማት ሥራ ጉብኝቶች እንደሚካሄድም ተመላክቷል።
በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን ለማጽናትና ልማትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን
Oct 29, 2025 181
ደብረ ብርሃን/ ገንዳ ውሃ/ደሴ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፡ - በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን ለማጽናትና ልማትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተናገሩ። በአማራ ክልል በደብረ ብርሃን፣ ገንዳ ውሃ እና ደሴ ከተሞች የሚገኙ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። ከደብረ ብርሃን ከተማ የውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ቀሲስ እሸቱ ተክለዮሃንስ እና አቶ ሁሴን ይመር፤ በከተማዋ አሁን ላለው ሰላምና ልማት የነዋሪውና የጸጥታ ሃይሉ የተቀናጀ ጥረት ውጤት መሆኑን አንስተዋል። የሰላም ጉዳይ ለማንም የማንተወው የጋራ አጅንዳችን ሆኖ ቀጥሏል ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ሰላምን ለማጽናትና ልማትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የከተማዋ የሀገር ሽማግሌ የሆኑት አቶ ለገሰ ሽፈራው፣ በበኩላቸው የሰላም ጥረታችን እና የልማት ትጋታችን ወደ ኋላ የማይመለስ ነው ብለዋል። በመሆኑም ለከተማዋና አካባቢው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥና ለተጀመሩ የልማት ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው በተለይም የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶችና አጠቃላይ ማህበረሰቡ ጠንካራ ተሳትፎና ትብብር በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳንኤል እሸቴ፤ ለማንኛውም ችግር መፍትሄዊ ሰላማዊ ውይይት መሆኑን በማመን መንግስት በዚህ ረገድ ብዙ እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ጥረት ውስጥ በተለይም የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው የሰላም ጥረቶችንና የልማት አቅሞችን መጠቀማችን ቀጣይነት ይኖረዋል ብለዋል። በተያያዘ ዜና በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ የሃይማኖት አባት መላዕከ ኃይል ፍሬው ዘመነ፤ በበኩላቸው የአካባቢያቸውን ሰላም በማስፈን የተጀመረው ልማት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከመቼውም ግዜ በላይ ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ሌላኛው የመድረኩ ተሳታፊ የሀይማኖት አባትና የሀገር ሽማግሌ ሼህ አደም ሱሌማን፤ የሀገሪቱን እድገት የማይፈልጉ የውጭ ጠላቶች እና የውስጥ ባንዳዎች ሰላምን ለማናጋትና ልማትን ለማደናቀፍ እየጣሩ ስለመሆኑ እንገነዘባለን ብለዋል። በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች ለሰላማችን መረጋገጥና እና ለልማታችን ቀጣይነት በጋራ ቆመን መስራት ይገባናል ሲሉ አስገንዝበዋል። በደሴ ከተማ በተካሄደው ተመሳሳይ መድረክ ላይ የተገኙት መላከ ብርሃን ቆሞስ አባ ተስፋሚካኤል፣ ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ለሰላም ግንባታ የምንሰስተው ነገር ሊኖር አይገባም ብለዋል። ከግጭትና ጦርነት ጉዳት እንጅ ጥቅም አለመኖሩን በተግባር አይተናል ያሉት አባ ተስፋሚካኤል ሰላማችንን በመጠበቅ የተጀመሩ ሰፋፊ የልማት ስራዎችን ከዳር ማድረስ ይጠበቅብናል ሲሉ አስገንዝበዋል። ሌላኛው የሐይማኖት አባት ሼህ ሀሽም መሀመድ፣ ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላም መስፈን ከመንግስት ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ ካሳው፤ የከተማውን ሰላም ከሕብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር አስተማማኝ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በከተሞቹ በተካሄደው ውይይት ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
መንግስት በተደጋጋሚ የሚያቀርበው የሰላም አማራጭ ለዘላቂ ሰላምና እድገት መረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው
Oct 29, 2025 192
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት በተደጋጋሚ የሚያቀርበው የሰላም አማራጭ የሚደነቅና ለዘላቂ ሰላምና እድገት መረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ጥያቄ አለን የሚሉ ቡድኖች በመንግስት የቀረበውን የሰላም አማራጭ በመቀበል ልዩነታቸውን በውይይት ለመፍታት መዘጋጀት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ትናንት መካሄዱ ይታወቃል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። መንግሥት ወደ ሰላም ከሚመጣ የትኛውም ኃይል ጋር አብሮ ለመስራት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በድጋሚ አረጋግጠዋል። በዚህም የሰላምና የጸጥታ ችግር ለሚስተዋልባቸው አንዳንድ አካባቢዎች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት መንግሥት ለሰላም አማራጭ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የምክር ቤቱ አባላት ላነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ መንግስት ሰላምን ለማጽናት ያለውን ቁርጠኝነት ተገንዝበናል ብለዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ፈቃዱ ጳውሎስ፤ ሰላም የሀገርን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማስቀጠል ሁነኛ መሳሪያ መሆኑን ገልጸዋል። ከሰላማዊ አማራጭ ውጪ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የሀገርን ልማትና ዕድገት በማደናቀፍ ዜጎችን ለእንግልት የሚዳርጉ መሆናቸውንም አንስተዋል። በዚህም የመንግስትን የሰላም ጥሪ ያልተቀበሉ ቡድኖች የሰላም አማራጭን በመቀበል አሉኝ የሚሏቸውን ጥያቄዎች በሰለጠነ መንገድ በውይይት መፍታት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። የሰላምን መንገድ በመምረጥ ህዝብና ሀገራቸውን በመካስ የሀገር ዕድገት አቅም እንዲሆኑም ነው የተናገሩት። በቀጣይም ለሀገር ሰላምና አንድነት በጋራ በመቆም የኢትዮጵያን ከፍታና የህዝብን ተጠቃሚነት በሚያስቀጥሉ የልማት ዘርፎች በትብብር መስራት አለብን ብለዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ሀቢብ አህመድ፤ ሰላም ለዜጎች ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ መሰረት መሆኑን ጠቅሰው ሁሉም ዜጋ የሰላም አርበኛ በመሆን ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት በጋራ መቆም እንዳለበት ገልጸዋል። ሀገራዊ የሰላም ግንባታ የሁሉንም ዜጋ ቀና ትብብር የሚጠይቅ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አያሌው ዘለቀ ጠቅሰዋል። ወይዘሮ ሸዋንብረት ማሞ በበኩላቸው፤ የሰላም አማራጭን ያልተከተሉ ወገኖች ምክክርን ሊያስቀድሙ ይገባል ብለዋል። የመንግስት የሰላም አማራጭ የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት ያስችላል ያሉት ወይዘሮ ሸዋንብረት፤ በጫካ የሚንቀሳቀሱ ወገኖችም የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ መክረዋል።
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)
Oct 29, 2025 223
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር በመሰረተ ልማት ያላትን ትስስር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላትም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በደቡብ ሱዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስቴር ፒዬንግ ዴንግ ኩኦል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ልዑካን ቡድኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን በተለይም በአቢዬ ግዛት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ገለጻ አድርጓል። ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አጠናቃ በስኬት በማስመረቋ ደስታቸውን በመግለጽ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት በህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ በመሳተፋቸውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በመሰረተ ልማት የበለጠ በመተሳሰር ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጎልበት ሊሰሩ እንደሚገባም መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ የሚገባትን የባሕር በር መጠየቋ ቅንጦት አይደለም - ምሁራን
Oct 29, 2025 191
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ መልማቷን ባልፈለጉ አካላትና ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በትላንትናው እለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቀይ ባሕር ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባሕር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ-ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን ኢትዮጵያ ታምናለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ የወሰነው ማን ነው ብለን ስንፈትሽ ማስረጃ አልተገኘም፤ ተቋማትም እንዳልገቡበት አንስተዋል። ባሕር በር የኅልውና ጉዳይ በመሆኑ ኢትዮጵያም ተዘግቶባት መኖር ስለማትችል ጥረቷ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን በጉዳዩ ላይ እንዳሉት ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን ባልፈለጉ አካላት በተንኮል የተነጠቀችውን የአካሏን ክፋይ መጠየቅ መብቷ እንጂ ቅንጦት እንዳልሆነ አስረድተዋል። የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ፤ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን ያጣችበት ሂደት ግፍ እንጂ ሕጋዊ አለመሆኑን አንስተው፤ መንግሥት ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት አምኖ አጀንዳ ማድረጉ ከሕግም ሆነ ከሞራል አንጻር ትክክል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ በዐሻጥር የተቀማችውን የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን ዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንድታጠናክርም መክረዋል። በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ ያሬድ አያሌው (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚ መሆን ፋይዳው የቀጣናውም ጭምር እንደሚሆን አስረድተዋል። ቀጣናውን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያ የጠየቀችው የአካሏን ክፋይና ህጋዊ መብት መሆኑን በመገንዘብ ለጋራ ተጠቃሚነት ሲሉ ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል።
ማህበራዊ
የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎትን ውጤታማ ለማድረግ ከልማት ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰራ ነው
Oct 30, 2025 75
ሃዋሳ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡- የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን ውጤታማነት ለማረጋገጥ ከልማት ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። በዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በእስራኤል የህክምና ቡድን አባላት የህጻናትና አዋቂዎች ነጻ የዓይን ቀዶ ህክምና አገልግሎት ዘመቻ ተጀምሯል። የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ፍስሃ ጌታቸው (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከ100 ከሚበልጡ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ ነው። የእስራኤል ኤምባሲ ማርሻ ከተሰኘ አለም አቀፍ የጤና ልማት ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ነጻ የዓይን ቀዶ ህክምና አገልግሎት ዘመቻም የዚሁ አካል ነው ብለዋል፡፡ ነፃ የህክምና አገልግሎቱ የክህሎት፣ የእውቀትና የልምድ ሽግግር በማድረግ የዩኒቨርሲቲውን የጤና ዘርፍ የልህቀት ማእከልነት ጅምር ስራዎችን ለማሳካት እንደሚያግዝም አመልክተዋል፡፡ የህክምና ቡድኑ 25 ሺህ ዶላር የሚገመት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን የገለጹት ደግሞ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ክብሩ ክፍሌ ናቸው፡፡ የህክምና ቡድኑ የሆስፒታሉ የዓይን ህክምና ክፍል ሃኪሞችን በማሰልጠን የእውቀት ሽግግር እንደሚያደርግም ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲው የዓይን ህክምና ክፍል ሃላፊ ዶክተር ተመስገን ተካ በበኩላቸው ለአምስት ቀናት በሚቆየው የዓይን ቀዶ ህክምና 60 የሚደርሱ ህጻናትና አዋቂዎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ገልጸዋል፡፡ አገልግሎቱ የዓይን መንሸዋረር፣ የዓይን ሞራ ግርዶሽና የዕይታ ችግር ላለባቸው ታካሚዎች ህክምና ከመስጠት ባሻገር የባለሙያዎች ልምድ ልውውጥ የሚደረግበት ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት የእስራኤል ምክትል አምባሳደር ቶሜርባር ላቪ በበኩላቸው እስራኤልና ኢትዮጵያ ዘመናትን የተሻገረ ወዳጅነት እንዳላቸው አስታውሰዋል፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል በትብብር ከሚከናወኑ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ጤና ቀዳሚው መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ የተጀመረው የዓይን ቀዶ ህክምና ዘመቻም የምርመራ፣ የቀዶ ጥገናና፣ የባለሙያ ስልጠናን ያካተተ መሆኑን አብራርተዋል። ከአሳሳና ከነንሰቦ ወረዳ የህክምና አገልግሎቱን ለማግኘት የመጡት አቶ ኢድርሲ ገነሞና ወይዘሮ ልደት አበበ የዓይን ህክምና ለማግኘት ወረፋ እየተጠባበቁ በነበረበት ወቅት በድንገት ይህን ህክምና ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ በአቅም ውስንነት ያጡትን የተሻለ የህክምና አገልግሎትን በነጻ ማግኘታቸው እንዳስደሰታቸው አስረድተዋል፡፡
ሠመራ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ነው
Oct 30, 2025 272
ሰመራ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡-ሠመራ ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮው ዓመት አዲስ የተመደቡለትን ተማሪዎች በመቀበል ላይ ነው። የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ፅህፈት ቤት ምክትል ዳይሬክተር አቶ አቡበከር ካሳው እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ባለፈው ዓመት ሬሚዲያል ተፈትነው ያለፉ እና በዚህ ዓመት አዲስ የተመደቡለትን 883 ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ነው። ዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማሩን ስራ ስኬታማ ለማድረግ የሚያስችሉ የመኝታና የመማሪያ ክፍሎች እንዲሁም የተለያዩ የትምህርት ቁሳቁሶችን በማሟላት በቂ ዝግጅት ማድረጉንም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የተቀበላቸው ተማሪዎች በ2017ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው የመግቢያ ነጥብ ያመጡና በሬሜዲያል መርሃግብር የማካካሻ ትምህርት ወስደው የመግቢያ ውጤት ያመጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው አቀባበል ካደረገላቸው ተማሪዎች መካከል ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመጣችው ተማሪ የውብዳር ተሰራ እንደተናገረችው ዩኒቨርሲቲው በጥሩ ሁኔታ አቀባበል አድርጎላቸዋል። በዩኒቨርሲቲው በሚኖራቸው ቆይታ የተሻለ ውጤት ለማምጣት ከጓደኞቿ ጋር በርትተው እንደሚያጠኑም ተናግራለች። ረጅም ርቀት አቆራርጠው ዩኒቨርሲቲው ሲደርሱ ደስ በሚያሰኝ ሁኔታ ተቀብለውን ማረፍ ችለናል ያለው ደግሞ ከሲዳማ ክልል ከሐዋሳ ከተማ የመጣው ተማሪ አቶቴ ኩማሎ ነው። ትምህርቱን በንቃት በመከታተል ውጤታማ ለመሆን ተግቶ እንደሚያጠናም ተናግሯል። በአቀባበል ስነ ስርዓቱ ላይ የዩኒቨርሲቲው አመራርና የተማሪዎች ተወካይ መገኘታቸው ታውቋል። ሠመራ ዩኒቨርሲቲ በአጠቃላይ 4ሺህ 600 ተማሪዎችን በማስተማር ላይ እንደሚገኝ ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
እውቅና እና ሽልማቱ ጠንክረን ለመማር የሞራል ስንቅ ሆኖናል
Oct 30, 2025 262
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡- የተሰጠን እውቅናና ሽልማት በቀጣይ ህይወታችን ጠንክረን ለመማር የሞራል ስንቅ የሚሆነን ነው ሲሉ በ2017 ዓ.ም ሀገር-አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የላቀ ውጤት ላዝመዘገቡ ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት አበርክቷል፡፡ እውቅናና ሽልማቱ የተበረከተው በመዲናዋ በሚገኙ ከመንግስት እና ግል ትምህርት ቤቶች ከ500 በላይ ውጤት ላስመዘገቡ 336 ተማሪዎች ናቸው። ከተሸላሚ ተማሪዎች መካከል ከጄኔራል ዋቆ ጉቱ ትምህርት ቤት ናኢም ለገሰ ለኢዜአ እንዳለው፤ በ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዶ 520 ነጥብ አምጥቷል፡፡ ለዚህ ውጤት የበቃው ጠንክሮ በመማሩ እና ለፈተና በቂ ቅድመ-ዝግጅት በማድረጉ መሆኑን ገልጿል፡፡ በዚህም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እጅ የታብሌት ሽልማት እንዳተበረከተለት ነው የተናገረው፡፡ የተበረከተለት ሽልማት በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ለሚፈልጋቸው የትምህርት ቁሳቁሶች ትልቅ ድጋፍ እንደሚሆነው ተናግሯል። ሀገር የሰጠችን እውቅናና ሽልማት በቀጣይ ህይወታችን ጠንክረን ለመማር የሞራል ስንቅ የሚሆንና መንግስት ለትምህርት ዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ግልጽ አድርጎ የሚያሳይ ነው ብሏል፡፡ በቀጣይ ጠንክሬ በመማር ሀገሬን በቴክኖሎጂ ዘርፍ ለማገልገል ከየትኛውም ጊዜ በላይ ዝግጁ ነኝ ብሏል፡፡ ከበሻሌ ትምህርት ቤት ሌላኛዋ ተሸላሚ ተማሪ እየሩሳሌም ያየሰው በበኩሏ፤ በ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳ 512 ነጥብ በማምጣት የታብሌት ሽልማት እንደተበረከተላት ተናግራለች፡፡ የተሰጣት እውቅናና ሽልማት በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ ጠንክራ እንድትማር የሞራል ስንቅ እንደሚሆናት ነው የገለጸችው፡፡ ሀገሯንና ህዝቧን በአውሮፕላን አብራሪነት የማገልገል ህልም እንዳላትም ተናግራለች፡፡ ከገላን የወንዶች አዳሪ ትምህርት ቤት እውቅና ያገኘው ዳዊት ፈይሳ በበኩሉ፤ በትምህርት ዘመኑ 580 ነጥብ 81 ውጤት እንዳስመዘገበ ገልጿል፡፡ ከከንቲባ አዳነች አቤቤ የታብሌት ሽልማት እንደተበረከተለት በመግለጽ፤ ይህም በቀጣይ ህይወቱ ይበልጥ እንዲማር መነሳሳት እንደፈጠረለት ተናግሯል፡፡ በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ኮምፒውተር ሳይንስ አጥንቶ ሀገሩን ማገልገል እንደሚፈልግ አመላክቷል፡፡ መንግስት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየወሰዳቸው ካሉ እርምጃዎች መካከል የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት ማበርከት አንዱ ነው፡፡
የገጠር ኮሪደር ልማት መሰረታዊ የአኗኗር ለውጥ ያየንበት ነው -አርሶ አደሮች
Oct 30, 2025 325
ወልቂጤ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡- የገጠር ኮሪደር ልማት መሰረታዊ የአኗኗር ለውጥ ያየንበት ነው ሲሉ በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቭ የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት በስፋት ተግባራዊ እየሆነባቸው ካሉ አካባቢዎች መካከል የጉራጌ ዞን አንዱ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማቱ አርሶ አደሩ አኗኗሩን እንዲያዘምን ከማድረግ ባለፈ ለዓመታት ባህሉ አድርጎ የቆየውን ተፈጥሮን የመንከባከብ ልምድ ይበልጥ እንዲጎለብት ያስቻለ ነው። የጉራጌ ማህበረሰብ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን ከጥንት ጀምሮ ሲያካሂድበት የቆየው "ጀፎረ" እየተጋረጠበት ያለው ሰው ሰራሽ አደጋን በመታደግ በኩልም የኮሪደር ልማቱ ትልቅ ሚና እየተወጣ ይገኛል። በመሆኑም ዘንድሮ በዞኑ በሚገኙ 273 የገጠር ቀበሌዎች የገጠር ኮሪደር ልማት ተግባራዊ እየተደረገ ነው። ልማቱ ከተተገበረባቸው አካባቢዎች አንዱ የሆነው እኖር ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ያጂቡ መሃመድ በገጠር ኮሪደር ልማት የሰውና የእንስሳት ማደሪያ ተለያይቶ በዘመናዊ መንገድ ለመኖር እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። በጓሯቸው እንሰት፣ አትክልትና ፍራፍሬ ከማልማት በተጨማሪ ዝርያቸው የተሻሻሉ የዳልጋ ከብት እያረቡ መሆኑንም ገልጸዋል። ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር አብድልመናን አህመድም የገጠር ኮሪደር ልማት አካባቢውን ውብ ከማድረግ ባለፈ በጓሯቸው ዶሮ በማርባት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በእንሰት ልማት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ነው የገለፁት። በወረዳው የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት የነዋሪውን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ የመስህብ ስፍራ እየሆነ መምጣቱን የገለጹት ደግሞ የወረዳው ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ጨዋነሽ ይልማ ናቸው። የገጠር ኮሪደር ልማት በአካባቢው የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማዘመን እያስቻለ መሆኑንም ተናግረዋል። የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው ጀፎረ ከጉራጌ ማህበረሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ጋር የተቆራኘ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከገጠር ኮሪደር ልማት ጋር በማስተሳሰር የማህበረሰቡን ኑሮ የሚለውጥ እንዲሆን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ማህበረሰቡ በአካባቢያዊ ልማት፣ በማህበራዊና መሰል ጉዳዮች ላይ በጋራ የሚመክርበትና አቅጣጫ የሚያስይዝበት መሆኑን ጠቅሰው፣ ያሉትን እሴቶች ከማስተዋወቅ ባለፈ ተሻጋሪ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። መንደሮቹ ቀላል ወጪ በሚጠይቁና የአካባቢውን ግብዓቶች በመጠቀም የሚሰሩ መሆናቸውን ጠቁመው፣ በዚህም አርሶ አደሩ ጤናማ ሕይወት እንዲኖር ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ በተለይ ምቹና ጽዱ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ አርሶ አደሩ ጓሮውን በተለያዩ አትክልት፣ ፍራፍሬና እንሰት ስለሚያለማ ጤናውን ለመጠበቅ በሚያስችለው መልኩ እየተሰራ ነው ብለዋል። የገጠር ኮሪደር ልማትን በዞኑ ሁሉም የገጠር ቀበሌዎች ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ላጫ አመልክተዋል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ክፍያ አማራጭ ለደንበኞቹ ምቹ አገልግሎት እየሰጠ ነው
Oct 30, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 2ዐ/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎች ክፍያ አማራጭ ለደንበኞቹ ምቹ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሆሊደይ፣ዲጅታል ሽያጭ እና ዓለም አቀፍ የደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ምክትል ፕሬዝዳንት ኃይለመለኮት ማሞ ገለጹ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኦንላይን የክፍያ አማራጭ ስርዓት አቅራቢ ከሆነው ቻፓ ካምባኒ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል። የመግባቢያ ሰነዱን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሆሊደይ፣ ዲጅታል ሸያጭ እና ዓለም አቀፍ የደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ምክትል ፕሬዝዳንት ኃይለመለኮት ማሞ እና የቻፓ ካምፓኒ መስራችና ስራ አስኪያጅ ናኤል ሃይለማሪያም ፈርመዋል። አቶ ኃይለመለኮት ማሞ በዚሁ ወቅት፤ አየር መንገዱ የደንበኞችን አገልግሎት ለማዘመን በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡ በዚህም በተለይ የአሰራር ስርዓቱን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በርካታ ለውጦችን አስመዝግበዋል ነው ያሉት፡፡ በዛሬው እለት ሀገር በቀል ቴክኖሎጂ ከሆነው ቻፓ ካምፓኒ ጋር የተደረገው ስምምነት የሀገር ውስጥና የውጭ ደንበኞችን የኦንላይን የክፍያ ስርዓት ይበልጥ ምቹ እና ቀልጣፋ የሚያደርግ ነው ብለዋል። ደንበኞች ሞባይል ባንኪንግን፣ቴሌ ብርንና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የበረራ ትኬቶቻቸውን በኦንላይን እንዲቆርጡ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎች ደህንነቱ የተጠበቀ ክፍያን ለመፈጸም ሁነኛ አማራጭ በመሆናቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እነዚህን ቴክኖሎጂዎች መጠቀሙን አጠናክሮ ይቀጥል፤ድጋፍም ያደርጋል ነው ያሉት። የቻፓ ካምፓኒ መስራችና ስራ አስኪያጅ ናኤል ሃይለማሪያም በበኩላቸው፤ ቴክኖሎጂው በኢትዮጵያ ውስጥ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ለአጠቃቀም ምቹ የሆነ የኦንላይን ክፍያ የሚሰጥ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ነው ብለዋል፡፡ ቴክኖሎጂው በኢትዮጵያ ውስጥ የኢ-ኮሜርስ ንግድ እንዲስፋፋ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል፡፡ ዓለም አቀፍ እና ከሀገር ውስጥ ደንበኞች ኦንላይን ክፍያዎችን መፈጸም እንደሚያስችል ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብት ምርታማነት ለማዘመን የተተገበሩ ቴክኖሎጂዎች የዜጎችን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ ነው
Oct 30, 2025 65
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብት ምርታማነት ለማዘመን የተተገበሩ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የዜጎችን የምግብ ዋስትና እያረጋገጡ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። ከዛሬ ጥቅምት 20 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሶስት ቀናት የሚቆይ የእንስሳት ሃብት ልማት፣ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን የሚያሳይ አውደ ርዕይና ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በአውደ ርዕይና ጉባኤው የተለያዩ ሀገራትን የወከሉ የግብርና ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የእንስሳት ሃብት ልማትና ተዋፅኦ ምርቶች፣ የዓሳና ንብ ማነብ ስራዎችን ለዕይታ ቀርበዋል። በዚሁ ወቅት በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አለማየሁ መኮንን (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብት ለማዘመን የተተገበሩ ቴክኖሎጂዎች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው። የሌማት ትሩፋትን ጨምሮ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ተግባራዊ የተደረጉ የእንስሳት ሃብት ልማት ስራዎች የዜጎችን ተጠቃሚነት እያሳደጉ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ለአብነትም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ከፍተኛ የእንስሳት ሃብት ምርታማነት የማሳደግ የዝርያ ማሻሻል ስራ በዜጎች ህይወት ላይ እመርታዊ ለውጥ ለማስመዝገብ ማስቻሉን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የኔዘርላንድስ አምባሳደር ክርስቲን ፕረን፤ የኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነት መርሃ ግብሮች የሀገሪቷን ዕድገት እየደገፉ ነው ብለዋል። የኔዘርላንድስ መንግስትም የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብትና የግብርና ምርታማነት ልማት የእሴት ሰንሰለት ለማሻሻል ለሚከናወኑ ጥረቶች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የፕራና ኢቨንትስ ማኔጅንግ ዳይሬክተር ነብዩ ለማ፤ አውደ ርዕዩ የኢትዮጵያን የእንስሳት ሃብት ምርታማነት የሚያሻሽል የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የግብዓት አቅርቦትና የገበያ ትስስርን መፍጠር ያስችላል ብለዋል። የአውደ ርዕዩ ተሳታፊ የሆኑት ዮዲት ቤተ-ማርያም፤ አውደ-ርዕዩ የወተት ማቀነባበሪያ ማሽነሪ ምርቶቻቸውን ለአርሶ አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ የገበያ ትስስርን ለመፍጠር ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው ገልጸዋል። ሌላኛው የአውደ ርዕዩ ተሳታፊ ማዕረግ ገብረ-እግዚአብሔር፤ አውደ ርዕዩ የማር ምርታቸውን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት መድረክ ነው ብለዋል። ከቻይና መጥተው የእንስሳት መኖ ማቀነባባሪያ ቴክኖሎጂን በአውደ ርዕዩ ያቀረቡት ዴቪን ሊዩ፤ ምርታቸውን ለኢትዮጵያና ተሳታፊ ሀገራት እያስተዋወቁ እንደሚገኙ ገልጸዋል። አውደ ርዕዩ የዶሮ ምርታማነትን የሚሻሽሉ ቴክኖሎጂዎችን በኢትዮጵያ ገበያ ለማቅረብ ዕድል ፈጥሮልናል ያሉት ደግሞ ከቱርክዬ በመምጣት የዶሮ ቤት በአውደ ርዕዩ ያቀረቡት ፉርከን ኤልማሊ ናቸው።
የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል የአካባቢውን አርሶ አደሮች ይበልጥ ውጤታማ እያደረገ ነው
Oct 30, 2025 66
ወራቤ ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ):- የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል የተሻሻሉ ዝርያዎችን በማቅረብ እና በሙያ ያደረገላቸው ድጋፍ የግብርና ልማታቸውን ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን እያገዛቸው መሆኑን በስልጤ ዞን የአሊቾ ውሪሮ ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል በዘር ብዜት፣ በምርምርና በቴክኖሎጂ ሽግግር የምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም ድጋፍ የተከናወኑ ሥራዎች በስልጤ ዞን አሊቾ ውሪሮ ወረዳ በመስክ ተጎብኝቷል፡፡ በዚህ ወቅት በወረዳው የሽልማት ቀበሌ አርሶ አደር ነስራ ከማል በሰጡት አስተያየት፤ ከዚህ ቀደም የግብርና ሥራቸውን በባህላዊ መንገድ ስለሚያከናውኑ በልፋታቸው ልክ ውጤታማ ሳይሆኑ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በምርምር ማዕከሉ የሚቀርበውን የሰብል ምርጥ ዘርና ሌሎች የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን በባለሙያዎች ታግዘው በመተግበር ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱንም ተናግረዋል፡፡ በዚህም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እየተሻሻለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ማዕከሉ በሰብል ዝርያና በሙያ በሚያደርግላቸው ድጋፍ ውጤታማነታቸው እያደገ መምጣቱን የተናገሩት ሌላው አርሶ አደር ናሲያ ጃቢር ናቸው፡፡ በተለይ በመስመር መዝራትን ጨምሮ ሌሎች የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን ተጠቅመው ከሚያለሙት ገብስ፣ ስንዴና አተር የተሻለ ምርት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዝርያዎቹ ፈጥነው ከመድረስ ባለፈ በምርት ይዘታቸው ከፍተኛና በሽታ መቋቋም የሚችሉ ናቸው ያሉት አርሶ አደሩ፤ በመሥመር መዝራቱም በተለምዶ በብተና ከሚደረገው አዘራር በተሻለ ውጤታማ እንዲሆኑ ያገዛቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደሥላሴ በወቅቱ እንዳሉት፤ የምርምር ማዕከሉ በክልሉ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያገዘ ነው፡፡ በዚህም በሌማት ትሩፋትና በአካባቢ ጥበቃ ሥራው ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ስለመሆኑ አንስተዋል፡፡ በምርምር ማዕከሉ እገዛ እየተገኙ ያሉ ስኬቶችን የማስፋት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ጉብኝቱ የምርምር ማዕከሉ ግብርናውን ለማዘመን የሚያከናውናቸው ሥራዎችን ለባለድርሻ አካላት የማሳወቅ፣ ግብዓት የማግኘትና ተሞክሮ መለዋወጥን ዓላማ ያደረገ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ያዕቆብ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ ማዕከሉ የስንዴ፣ ገብስ፣ ቦሎቄ፣ ተልባ፣ እንሰትና የእንስሳት ዝርያን ማሻሻል ጨምሮ ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነት ለማሻሻል የሚያግዙ ተግባራት ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በጉብኝቱ ላይ የክልሉ ግብርና፣ ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ አመራሮች እና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል፡፡
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ጥቅሟን እና ህልውናዋን ለማስጠበቅ ወደነበረችበት ቀይ ባህር መመለሷ ግድ ነው
Oct 30, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ጥቅሟን እና ሕልውናዋን ለማስጠበቅ ወደነበረችበት ቀይ ባህር መመለሷ ግድ ነው ሲሉ ፕሮፌሰር ብሩክ ሀይሉ በሻህ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በኢትዮጵያና አሜሪካ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ብሩክ ሀይሉ በሻህ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ከባህር በር በ60 ኪሎሜትር ርቀት የበይ ተመልካች ለመሆን ተገዳለች፡፡ ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር የተገለለችበት መንገድ ህጋዊ መሰረት የሌለው መሆኑን በማንሳት፤ ባህር በር አልባ ከሆኑ 44 ሀገራት ሰፊ የህዝብ ቁጥር እንዳላትም ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለቀይ ባህር ቀጣና አዲስ አይደለችም ያሉት ፕሮፌሰር ብሩክ፤ ከፐርሺያ እስከ ባበል መንደብና ሕንድ የሚቀዝፉ ጠንካራ መርከቦች እንደነበሯት አስታውሰዋል፡፡ የቀይ ባህር ባለቤት በነበረችበት ወቅት ከሮማና ግሪክ ግዛቶች ጋር ጠንካራ የንግድ ትስስር እንደነበራት ገልጸው፤ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ጥቅምና ሀገራዊ ህልውና ለማስጠበቅ ወደ ቀይ ባህር መመለስ ግድ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በትብብር ላይ የተመሰረተ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ እንዳላት በመጥቀስ፤ ወደ ቀይ ባህር መመለስ ለቀጣናው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ በዓለም ላይ የባህር በር ከሌላቸው ሀገራት መካከል 16ቱ በአፍሪካ እንደሚገኙ ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ከ34 ዓመት በፊት ሁለት ሺህ ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የባህር በር ባለቤት ነበረች ብለዋል፡፡ ከአፍሪካ ዙምባብዌና ማላዊ የሞዛምቢክን የባህር በር እንደሚጠቀሙ አስታውሰው፤ ኢትዮጵያ ያቀረበችው ሰላማዊና ህጋዊ ጥያቄ በጎረቤት ሀገራት በቅንነት ሊታይ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ህልውናዋን ለማስጠበቅ ዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ድረስ መሄድ የሚያስችላት ህጋዊ ማዕቀፍ በግልጽ እንዳለም ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር እንዳትጠቀም ለመከልከል መብት ያለው የለም ያሉት ፕሮፌሰር ብሩክ፤ የባህር በር ያለው ሀገር የመተባበር ግዴታ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ በተከተለችው ሰላማዊ አካሄድ የባህር በር እንደሚያስፈልጋት ሀያላን ሀገራት ጭምር የተቀበሉት እውነት ሆኗል ብለዋል፡፡ ለኢትዮጵያ የባህር በር ተገቢነት ከአውሮፓ እስከ ባህረ ሰላጤው ሀገራት እውቅና መስጠት መጀመራቸው፤ የዲፕሎማሲያዊ ጥረት ፍሬ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በክልሉ የግብርና ምርምር ማዕከላት ግብርናን በማዘመን ለዘርፉ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ አድርገዋል - ቢሮው
Oct 30, 2025 73
ወራቤ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ምርምር ማዕከላት ግብርናን በማዘመን ለዘርፉ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል ለስርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም በዘር ብዜት፣ በምርምርና በቴክኖሎጂ ሽግግር ባከናወናቸው ተግባራት ላይ የመስክ ምልከታ ተካሂዷል። የቢሮው ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ ዓለምይርጋ ወልደስላሴ በዚህ ወቅት እንዳሉት በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ምርምር ማዕከላት ተጨማሪ አቅም እየሆኑን ነው። በግብርና ዘርፍ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በራስ አቅም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ከተረጂነት ለመወጣት እየተደረገ ባለው ጥረት ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል። በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ ዐሻራና በሌሎች የግብርና ሥራዎችም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት በማሳደግ በኩል ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ነው የጠቆሙት። ባለፈው ዓመት በክልሉ በበልግ፣ በመኸርና በበጋ መስኖ ልማት 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር ማሳ በማልማት 142 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ገልጸዋል። ለዚህም የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርጥ ዘር ብዜት፣ የተሻሻሉና በምርምር የተደገፉ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በማሸጋገር ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አስታውሰዋል። በዚህ ዓመትም 159 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ግብ ተጥሎ ወደ ተግባር መገባቱን ነው ምክትል ቢሮ ኃላፊው የተናገሩት። የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ያዕቆብ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ የግብርና ልማት ሥራውን የሚያግዙ ተግባራት በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የሀገራዊና ክልላዊ ኢንሼቲቮች ትግበራን በምርምርና በቴክኖሎጂ እያገዘ እንደሚገኝም ነው የገለጹት። የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ቀድራላ ዋበላ(ዶ/ር) እንዳሉት ማዕከሉ ግብርናን ማዘመን የሚያስችል የምርምር፣ የዘር ብዜትና ቴክኖሎጂን የማስተዋወቅ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የአካባቢን ስነ ምህዳር መሰረት በማድረግ የዘር ብዜት፣ የሰብል ጥበቃና እንስሳት ዝርያ ማሻሻልን ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመስክ ምልከታው የክልሉ ግብርና ቢሮ፣ የምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ አመራሮችና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።
ለኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት አቅም የሚሆን የሰው ሃይል እያፈራን ነው -ኢንስቲትዩቱ
Oct 30, 2025 80
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡- ለኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት አቅም የሚሆን የሰው ሃይል እያፈራ እንደሚገኝ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ገለጸ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ማብራሪያቸው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ፕሮጀክቶቸ ዕውን መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያም ሀገርን ከጸጋዎቿ በማሰናሰል በብዝኅ የኢኮኖሚ ልማት ዕመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ ያስቻሉ የአሰራር ሥርዓቶች መዘርጋታቸውን አስረድተዋል። በማዕድን ዘርፍም የተፈጥሮ ጋዝ፣ ነዳጅና ሌሎች የማዕድን ጸጋዎችን በማልማት የኢትዮጵያን ዕድገት ወደተሻለ ማዕራፍ የሚያሸጋግሩ ግዙፍ ብሔራዊ ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን አብራርተዋል። የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ዕመርታ ለማስቀጠል ከዳንጎቴ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር የተጀመረው የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካም የአርሶ አደሩን የግብዓት አቅርቦት ፍላጎት እንደሚፈታ አንስተዋል። ኢትዮጵያን የአፍሪካ የአቬየሽን ኢንዱስትሪ ማዕከል የሚያደርጋት የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ፕሮጀክትን በተቀመጠለት የግንባታ ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ብሩክ ከድር (ዶ/ር)፤ በትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ንድፈ ሃሳብን ከተግባር በማዋሐድ ዕውቀትና ክህሎት የተላበሰ የሰው ሃይል እያፈሩ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ኢንስቲትዩቱ የሚያፈራው የሰው ሃይልም ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ ስኬታማነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት ከ400 በላይ ብቁ የብረታ ብረት ብየዳ ሙያተኞችን አሰልጥኖ በማሰማራት ገንቢ ሚና መወጣቱን አስረድተዋል። በቀጣይም በዕውቀትና ክህሎት መር ትምህርትና ስልጠና በተለያዩ መርሃ ግብሮች ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ስኬት አቅም የሚሆን የሰው ሃይል የማፍራት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። አዳዲስ ስልጠና መርሃ ግብሮችን በመቅረጽ ጭምር በግብርና ማቀነባበር፣ ሥነ-ውበት፣ በቆዳና ሌጦ ተያያዥ የኢንዱስትሪ መስኮችም ብቃት ያላቸው ሙያተኞችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝ አንስተዋል። በፕላስቲክ ቴክኖሎጂ፣ በተሽከርካሪ ጥገና ዘርፎችም የትምህርትና ስልጠና መርሃ ግብር በመስጠት የዘርፉን ዕድገት የሚደግፍ የሰው ሃብት እንደሚያፈሩ ገልጸዋል። በመጨረሻም በቅርቡ የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አስፈላጊ የሆኑ ሙያተኞችን ማፍራት የኢንስቲትዩቱ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢንስቲትዩቱ በዚህ ላይ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
በክህሎት ኢትዮጵያ መርሃ ግብር በቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች እየተገኙ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
Oct 29, 2025 144
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ በክህሎት ኢትዮጵያ መርሃ ግብር በቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ከወጣቶች ጋር በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን የስራና ከህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የተመረቱ የተኪ ምርት ቴክኖሎጂዎች ማስተዋወቂያ ፕሮግራም እየተካሄደ ይገኛል። ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ችግሮችን ወደ ዕድል ለመቀየር ከሚተጉ ወጣቶች ጋር የሚከናወኑ ተግባራትን በማጠናከር ኢትዮጵያን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እየተሰራ ነው። ባለፉት ሁለት ዓመታት በተካሔደው በክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም የቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ስራዎች ከወጣቶች ጋር በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች እየተገኙ ነው ብለዋል። ችግር ፈቺና በርካታ ስራዎችን ማከናወን የሚያስችሉ አማራጮች ያሏቸው ቴክኖሎጂዎች በስፋት እየተመረቱ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም የፈጠራ ሰራዎችን ወደ ምርት ለማስገባት የግሉ ዘርፍ በስፋት እንዲሰማራም ጠይቀዋል። በዛሬው እለት በተካሔደው መርሃ ግብር ላይ የቀረቡት ቴክኖሎጂዎች በመደመር እሳቤ ክህሎትና እውቀትን በጋራ መምራት እንደሚቻል የሚያመላክቱ ናቸው ብለዋል። የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ፈጠራን ማበረታታት ፍጥነትን ማሳደግ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነን ሲሉም ገልጸዋል። በኢንስቲትዩቱ ለመጀመሪያ ጊዜ አዳዲስ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች መመረታቸውንም ተናግረዋል። ለአብነትም ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንዳክሸን ሞተር መሰራቱን ፣ የኤሌትሪክ ተሸከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ቴክኖሎጂ ፣ ስማርት የመንገድ ዳር መብራቶች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል። በቴክኖሎጂ ማስተዋወቂያ መርሃ ግብሩ ላይ ስራዎቻቸውን ካቀረቡት መካከል በኢንስቲትዩቱ የቴክኖሎጂ ዲፓርትመንት ቴክኖሎጂ ዴስክ ሀላፊ አቶ ወጋየው ሙሉነህ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንዳክሸን ሞተር መስራቱን ገልጸው፤ ፈጠራውን ማንኛውንም ሞተር ማንቀሳቀስ የሚያስችል ለኢንዱስትሪዎች ትልቅ ጠቀሜታ ያለውና የውጭ ምንዛሬ ወጪን መቀነስ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። በቴክኖሎጂ ፈጠራ የተሰማራው ወጣት አቤል ማሰረሻ በበኩሉ ስማርት የመንገድ ዳር መብራቶች መስራቱን ገልጾ ዘመናዊ ቴክኖሎጂው ከመብራት አገልግሎት በተጨማሪ ካሜራና ሌሎች ሴንሰሮች ያለው በመሆኑ መረጃ እንደሚሰበሰብም ጠቁሟል።
የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ያሳድጋል
Oct 28, 2025 457
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ፋይዳው የጎላ መሆኑን በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። በቅርቡ ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት ከሀይል አማራጭነት የዘለለ የተለያዩ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ከእነዚህ ጠቀሜታዎች መካከል አንዱ የኒኩሌር ህክምና አገልግሎት ይገኝበታል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መምህር፣ ሀኪም፣ ተመራማሪና የካንሰር ሕክምና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን ሁነኛው ለኢዜአ እንደገለፁት የኒኩሌር ፕላንቱ በሕክምናው ዘርፍ ለኢትዮጵያ ትልቅ እድል ይዞ የሚመጣ ነው። በተለይ በዋናነት የካንሰር በሽታን ለማከም ያለው ፋይዳ ላቅ ያለ በመሆኑ የህክምና አገልግሎቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደርሰዋል ብለዋል። አክለውም ለራዲዮ ቴራፒ ሕክምና የሚውሉ መድሀኒቶችን ለማምረትና የቆይታ ጊዜያቸው ከስምንት ቀን የማይበልጡ መድሀኒቶችን ብልሽት መፍታት ያስችላል ነው ያሉት። ከኒኩሌር ጋር በተያያዘ መንግስት የወሰደው ኢንሼቲቭ ከህክምና አገልግሎቱ ባለፈ በዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያለው ፋይዳም ከፍተኛ በመሆኑ መበረታታት እንዳለበት ዶክተር ሰለሞን ተናግረዋል። ሌላው የዩኒቨርሲቲው መምህርና የህጻናት ካንሰር ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሙሉአለም ንጉሴ በበኩላቸው ያደጉ ሀገሮች የኒኩሌር ሕክምናን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠቀሙበት አንስተዋል። የኒኩሌር ሀይል ለአዋቂም ሆነ ለሕጻናት ሕክምና የበሽታውን ሁኔታና ያለበትን ደረጃ ለይቶ ለማከም ያለው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ፕሮጀክቱ ለሕክምናው ዘርፍ ጭምር ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ብለዋል። የኒኩሌር ሀይል ለካንሰር ሕክምና አገልግሎት ሦስት ዋና ዋና ፋይዳ አለው ያሉት ባለሙያው የካንሰር አይነቱንና የስርጭቱን መጠን እንዲያውቅ ይረዳዋል ነው ያሉት። ሕመምተኛውም የበሽታው አይነትና ስርጭትን መሰረት ያደረገ ሕክምና እንዲያገኝ እንደሚያስችለው ገልጸዋል። ለካንሰር ሕሙማን የኒኩሌር ሕክምና በሀገር ውስጥ ስለማይሰጥ ሕክምናውን ለማግኘት ወደ ውጪ እንደሚላኩ የገለጹት ዶክተር ሙሉአለም በዚህም ምክንያት ለወጪና እንግልት ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል። የኒኩሌር ሕክምና ከሌሎቹ የሲቲ ስካን፣ ኤም አር አይ እና ሌሎች መሳሪያዎች አንጻር ያለውን በሽታ ለይቶ ማሳየት ብቻ ሳይሆን ያደረሰውን የጉዳት መጠን ጭምር ለይቶ የሚያሳይ ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የሕክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ክብሩ ክፍሌ ናቸው። በካንሰር የተጠቃ የሰውነት አካል ምን ያህል እንደተጎዳ፣ የትኛው ክፍሉ ሥራውን በአግባቡ እያከናወነ እንደሚገኝ የሚለውን በትክክል መለየት የሚያስችል የዘመናዊ ሕክምና ትልቅ መሳሪያ መሆኑን አስረድተዋል። እንደ ሀገር ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ከፍ ወዳለ ደረጃ የሚያሸጋግር በመሆኑ መንግስት የወሰደው ተነሳሽነት ሊበረታታና ሊደገፍ ይገባል ሲሉም ምሁራኑ ገልፀዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ምድቡን መቀላቀል ሳይችል ቀርቷል
Oct 30, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ሁለተኛ ዙር ከወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒራሚድስ ጋር ዛሬ ባደረገው የመልስ ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፏል። ማምሻውን በጁን 30 ኤር ዲፌንስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሙስጠፋ ዚኮ እና ኤወርተን ዳ ሲልቫ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳረፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ፒራሚድስ በድምር ውጤት 3 ለ 1 በማሸነፍ ምድብ ድልድሉን መቀላቀል ችሏል። ክለቦቹ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ አንድ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ መድን የመጀመሪያ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው ሁለተኛ ዙር ላይ ተገቷል። ቡድኑ አምናው በታሪኩ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ማሸነፉን ተከትሎ ነው በአህጉራዊ መድረክ የመሳተፍ እድል ያገኘው። የግብጹ ፒራሚድስ ክለብ የወቅቱ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ የዋንጫ ባለቤት ነው።
በሊጉ ድሬዳዋ ከተማ ሲያሸንፍ አዳማ ከተማ ከሀዲያ ሆሳዕና አቻ ተለያይተዋል
Oct 30, 2025 66
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ተካሄደዋል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታን 2 ለ 1 አሸንፏል። አሰጋኸኝ ጴጥሮስ በ31ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ግብ መቀሌ 70 እንደርታ መሪ ሆኗል። መሐመድ ኑር ናስር በ49ኛው እና አቤል አሰበ በ93ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፏቸው ጎሎች ድሬዳዋ ከተማን አሸናፊ አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ በስድስት ነጥብ ደረጃውን ወደ ሰባተኛ ከፍ አድርጓል። መቀሌ 70 እንደርታ በአንድ ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል። በተያያዘም አዳማ ከተማ ከሀዲያ ሆሳዕና በአዲስ አበባ ስታዲየም ያደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አዳማ ከተማ በሶስት ነጥብ 11ኛ፣ ሀዲያ ሆሳዕና በሁለት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የሶስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የአራተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ መድን ከግብጹ ፒራሚድስ ጋር ዛሬ የመልስ ጨዋታውን ያደርጋል
Oct 30, 2025 110
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ሁለተኛ ዙር የመልስ ጨዋታውን ዛሬ ከወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒራሚድስ ጋር ያከናውናል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ካይሮ በሚገኘው ጁን 30 ኤር ዲፌንስ ስታዲየም ይካሄዳል። ክለቦቹ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ብሩክ ሙሉጌታ ለኢትዮጵያ መድን፣ ፊስተን ማዬሌ ለፒራማድስ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኢትዮጵያ መድን በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ድልድልን ይቀላቀላል። መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ሲሳተፍ የዘንድሮው የመጀመሪያው ነው። ቡድኑ አምናው በታሪኩ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ለመጀመሪያ ጊዜ በማሸነፍ በአህጉራዊ ውድድሩ የሚያሳትፈውን እድል እንዲያገኝ አስችሎታል። የግብጹ ፒራሚድስ ክለብ የወቅቱ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ የዋንጫ ባለቤት ነው። ክለቡ የካፍ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫንም አንስቷል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሶስተኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል
Oct 30, 2025 72
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። አዳማ ከተማ ከሀዲያ ሆሳዕና ከቀኑ 9 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በሊጉ ባደረጋቸው ሁለት ጨዋታዎች ሁለት ነጥብ ብቻ ያገኘው አዳማ ከተማ በሁለት ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሀዲያ ሆሳዕና በአንድ ነጥብ 18ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ቡድኖች በ2017 ዓ.ም በሊጉ ባደረጓቸው የእርስ በእርስ ጨዋታዎች በተመሳሳይ አንድ አንድ ጊዜ አሸንፈዋል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ድሬዳዋ ከተማ ከመቀሌ 70 እንደርታ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ድሬዳዋ ከተማ በሶስት ነጥብ 10ኛ፣ መቀሌ 70 እንደርታ በአንድ ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ጨዋታው ድሬዳዋ ከተማ ተከታታይ ድሉን ለማግኘት፣ መቀሌ 70 እንደርታ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታሉ። ቡድኖቹ በ2017 ዓ.ም በሊጉ በነበራቸው የእርስ በእርስ ግንኙነት መቀሌ 70 እንደርታ አንድ ጊዜ ሲያሸንፍ በቀሪው ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው
Oct 29, 2025 129
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚችል ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደርና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ አኒል ኩማር ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በብዝሃ የአየር ንብረት የታደለች፤ ልዩ ልዩ የተፈጥሮ ሀብቶችን የያዘች፣ በርካታ እፅዋቶችና የዱር እንስሳት ዝርያዎች የሚገኙባት መሆኗን አምባሳደሩ ተናግረዋል፡፡ አምባሳደሩ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚችል ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ የአገሪቱን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ ለብዝሃ ህይወት መጎልበት ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ስራው አስደናቂ መሆኑን ተናግረዋል። በአፋር ክልል የሚገኘው ዝቅተኛው የደናክል በረሃ እና የተለየ የአየር ንብረት ያለው የስምጥ ሸለቆ መነሻ ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ አረንጓዴ የሆኑና ከፍተኛ የዝናብ መጠን የሚያገኙ ደጋማ አካባቢዎችን የያዘች መሆኗንም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያሉ ልዩ ልዩ የአየር ንብረት ጸባዮች፣ የዕጽዋትና የዱር እንስሳት ዝርያዎች ሀገሪቱን ብዝሃ ተፈጥሮ የተቸራት አድርጓታል ብለዋል፡፡ ይህም የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስፋት ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አመላክተዋል፡፡ አምባሳደሩ በኢትዮጵያ የተተገበሩ እንደ አረንጓዴ አሻራ ያሉ መርሃ-ግብሮችና ሰፋፊ የልማት ስራዎች ለሀገሪቱ የወደፊት ብልፅግና ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው ጠቅሰው ፤ የተተከሉት ዛፎች እንዲጸድቁ የሚደረገውን እንክብካቤ አድንቀዋል። በቀጣዩች አስር ዓመታት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደማሚ ለውጦችን ታስመዘግባለች ሲሉም ገልጸዋል። ህንድ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ለምታከናውነው ተግባር አድናቆት እንዳላት ጠቁመው፤ አገራቸው በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ አስፈላጊነት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ አቋም እንዳላት ተናግረዋል፡፡ ህንድ እና ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ የጋራ ስምምነት እንዳላቸው አስታውሰው፡ ትብብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ያከናወነቻቸው ተግባራት የአዕዋፋትንና የዱር እንስሳትን ስደት ትርጉም ባለው መልኩ መቀነሱ ይታወቃል፡፡
በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደናቂ የልማት ስኬት ማስመዝገብ ተችሏል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Oct 28, 2025 147
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡-በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደናቂ የልማት ስኬት ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው። በመደበኛ ስብሰባው ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምላሽና ማብራሪያቸው፤ 2017 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ የታሪክ እጥፋት ውስጥ ይቻላሉ ተብሎ የማይታሰቡ ጉዳዮች የተቻሉበት የስኬት ዓመት እንደነበር ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ያነገባቸውን ዓላማዎችና ያስገኛቸውን ውጤቶች አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአንድ ዘርፍ ላይ ተንተርሶ ከድህነት ሊወጣ አይችልም በሚል ብዝኅ ዘርፍና ብዝኃ ተዋናይ የኢኮኖሚ አቅጣጫ ላይ የተነደፈው ፖሊሲ በእጅጉ ውጤታማ እየሆነ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎች ሳይዘነጉ አምስቱ ግንባር ቀደም የተሰናሰሉ በብዝኅ ዘርፍ ቢመሩ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እንደሚያሻሽሉ እምነት መጣሉን አስረድተዋል። ግብርና እና ማዕድን ለኢንዱስትሪ ግብዓት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ ኢንዱስትሪውም ግብርናን የሚያፋጥን ማሽን ፈጣሪ ነው ብለዋል። ቴክኖሎጂ የታከለበት ብዝኅ ዘርፍ የኢኮኖሚ ልማትም ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ያስቻለ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ እንደሚገኝ አንስተዋል። የብዝኅ ተዋናይነትም መንግስት አንድ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ በመሆን ከግሉ ዘርፍ፣ ከህዝብና የልማት አጋሮች ጋር ተሳስሮ የኢትዮጵያን ልማት በየፈርጁ ማፋጠን አለበት የሚል እምነት መያዙን ገልጸዋል። የግልና መንግስት አጋርነት እሳቤ ያለ ቢሆንም የመንግስትና ህዝብ አጋርነት ግን ግልጽ አቅጣጫ የተቀመጠለት ከለውጡ በኋላ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም በመንግስት የህዝብ አጋርነት ኢትዮጵያ በርካታ ስኬቶች ማስመዝገቧን ጠቅሰው፤ ለዚህም የአረንጓዴ አሻራ 48 ቢሊየን ችግኞች ስኬት ማሳያ ነው ብለዋል። እያንዳንዱ ችግኝ ከጅምሩ እስከ ተከላ መርሃ ግብሩ ባለው ሂደት አንድ ዶላር ቢወስድ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ 48 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስት ማድረግ መቻሏን አስረድተዋል። በዚህም ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ያለመታከት ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን በመስጠት በየዓመቱ ስለሰሩ ይህን ያክል ሃብት ያስወጣ የነበረን ስራ በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር ማሳካት ተችሏል ብለዋል። በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ የሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለቀጣናው ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ልማት እንዲሁም ለጋራ ብልፅግና መሪ ሚና እየተወጣች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Oct 27, 2025 193
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 17/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለቀጣናው ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ልማት እንዲሁም ለጋራ ብልፅግና መሪ ሚና እየተወጣች ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 2ኛውን የኢትዮጵያ የውሃ እና ኢነርጂ ሳምንት በሳይንስ ሙዚየም አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል፣ ለውሃ እና ለአረንጓዴ ልማት በሰጠችው ትኩረት ለውጥ እያመጣች ሚሊዮኖችን ተጠቃሚ እያደረገች መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የቀጣናው የኃይል ማዕከል እየሆነች ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለጂቡቲ፣ ለሱዳንና ለኬንያ ታዳሽ ኃይል እያቀረበች ነው ብለዋል። በቅርቡም ወደ ሌሎች ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እንደምትልክ ጠቅሰው፥ ይህም የጋራ ቀጣናዊ የብልጽግና ራዕይዋ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዚህ የላቀ ራዕይ ምሰሶ እንደሆነ ገልጸው፥ ግድቡ ጽናታችንን፣ አንድነታችንንና በአፍሪካ መጻኢ የጋራ ህልሞች ላይ ያለንን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል። የግድቡ አገልግሎት ከኃይል ልማት ባሻገር ለብዝኃ ህይወት ጥበቃ፣ ጎርፍን ለመከላከልና በታችኛው ተፋሰስ ላሉ ሀገራት የተስተካከለ የውሃ ፍሰት እንዲያገኙ ያስችላል ነው ያሉት። ከፉክክር ይልቅ የጋራ ተጠቃሚነትንና ትብብርን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን በማንሳትም፥ ኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞቿ የቀጣናው የትስስር መሠረቶች ናቸው በሚል ግልፅ አቋም እየሠራች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ለአብነትም በአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ ግብር ባለፉት ዓመታት ከተተከሉ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች አንድ ሦስተኛ ያህሉ በዓባይ ተፋሰስ መተከላቸውንና ይህም ለሌሎች ሀገራት ፋይዳው የላቀ መሆኑን አስረድተዋል። በሌላ በኩል ኢኮኖሚያችን እያደገ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የባህር በር ማግኘት ለቀጣይ እጣፈንታችን ዋስትና የሚሰጥ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የባህር በር ለኢትዮጵያ የግድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የባህር በር ማግኘት ንግድን ለማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ውህደትን ለማጎልበትና ቀጣናዊ ትብብርን ለማሳደግ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር እጣፈንታዋ የተሳሰረ በመሆኑ በጋራ ለመልማት እና ዘላቂ ጥቅምን ለማስጠበቅ በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት እየሠራች ነው ብለዋል። አፍሪካ ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ዋስትናዋን እንድታረጋግጥ ኢትዮጵያ መሪ ሚናዋን መወጣቷን እንደምትቀጥልም አረጋግጠዋል።
እምቦጭን በዘላቂነት ለመከላከል የህብረተሰብ ተኮር ሥራ ውጤት እያስገኘ ነው
Oct 26, 2025 240
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ)፡-እምቦጭን በዘላቂነት ለመከላከል የህብረተሰብ ተኮር ሥራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ ሞቱማ መቃሳ ገለጹ፡፡ በውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ ሞቱማ መቃሳ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ያቀደቻቸውን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች ለማከናወን የውኃ ሀብቷን መጠበቅ ወሳኝ ነው። ስለሆነም መንግስት በአገሪቷ የልማት እቅዶች ውስጥ የውኃ አስተዳደርና ጥበቃን ቅድሚያ ሰጥቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ለአብነትም በአገሪቷ ውስጥ ምን ያህል የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውኃ ሀብት እንዳለ በትክክል የመለየትና የመመዝገብ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህን ሀብት ለየትኞቹ የልማት ዘርፎች በምን ያህል መጠንና ጥራት ለማዋል እንደሚቻል የውኃ አቅም ልየታ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የውኃ ሀብት አስተዳደርና ጥበቃ ስራ ከፍ ብሎ እንዲመራ ሚኒስቴሩ መዋቅራዊ ማሻሻያ ማድረጉንም አመልክተዋል። ከፍተኛ ትኩረት ከሚሹ የውኃ አካላት ጥበቃ ጉዳዮች መካከል አንዱ በእምቦጭ አረም ምክንያት የሚከሰተውን ችግር ማቃላል መሆኑን አመልክተዋል። እምቦጭ በፍጥነት የሚስፋፋና በየጊዜው ተመልሶ የሚመጣ መሆኑን ያወሱት አቶ ሞቱማ፤ በዘላቂነት ለማቃለል በየጊዜው አስቸጋሪ ፈተና መሆኑን አንስተዋል። ይህንን ችግር መፍትሄ ለመስጠት ሚኒስቴሩ በትኩረት እየሰራበት እንደሚገኝም አብራርተዋል። ይህን ዘላቂ ችግር ለማቃለል ህብረተሰብን ያማከለ አሰራር ተቀይሶ በመተግበር ላይ እንደሚገኝና ውጤትም እየተገኘበት እንደሆነም አስታውቀዋል። በጣና ሐይቅና በሌሎች የውኃ አካላት ላይ የእምቦጭ አረምን ችግር ለመፍታት ከተጀመሩ ሥራዎች በተጨማሪ ህብረተሰብ ተኮር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ሞቱማ ተናግረዋል። የውኃ ሀብት ጥበቃና አስተዳደር የሀገር ጉዳይ በመሆኑ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና መላው ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው
Oct 24, 2025 355
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡ ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡ በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀመረ
Oct 24, 2025 242
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦11ኛው የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተሞች በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው። በፎረሙ ላይ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች ምክክር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በቀጣናው መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከል የተጀመሩ የቅንጅት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኢጋድ
Oct 20, 2025 444
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። የኢጋድ ሶስተኛው የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት የሚኒስትሮች ስብሰባ ዛሬ በኬንያ ናይሮቢ ተጀምሯል። “በኢጋድ ቀጣና ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሰራተኛ ፍልሰት እና የሰዎች ዝውውር ህጋዊ ማዕቀፍን ማሻሻል” የስብሰባው መሪ ቃል ነው። በስብሰባው ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት የሰራተኛ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች፣ ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(አይኤልኦ)፣ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት(አይኦኤም)፣ የአውሮፓ ህብረትና የልማት አጋሮች ተገኝተዋል። በኢጋድ ቀጣና የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በቀይ ባህር መስመር ያለውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ከኢጋድ ቀጣና ውጪ የሚገኙ ዜጎች አባል ሀገራትን በነጠላ የመግቢያ ቪዛ መጎብኘት የሚያስችላቸውን የቪዛ ኢኒሼቲቭ ይፋ ይደረጋል። ኢኒሼቲቩ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርና ድንበር ተሻጋሪ ንግድን ማሳለጥ እንዲሁም ቱሪዝምን የማሳደግ ፋይዳ እንዳለው ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአውሮፓ ህብረት የፋይናንስ ድጋፍ የሚተገበረው ነጻ የሰዎችና የቁም እንስሳት እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፍ ሁለተኛ ምዕራፍ ይፋ ይሆናል። ማዕቀፉ ህጋዊ የፍልሰት መንገዶች ለማጠናከር እና ቀጣናዊ ትስስርን የማሳካት ግብ ያለው መሆኑንም አመልክቷል። ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ሰንሰለትን መበጣጠስ፣ በፍልሰት በሌላ ሀገር የሚገኙ ዜጎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ላይ ምክክር ያደርጋሉ። በውይይቱ ማብቂያ ሀገራት የጋራ መግለጫ እንደሚያወጡ የሚጠበቅ ሲሆን ደህንነቱ የተጠበቀ መደበኛ ፍልሰት፣ ጠንካራ የሰራተኛ አስተዳደር ስርዓት መፍጠርና ለሰዎች ዝውውር የተቀናጀ ቀጣናዊ ምላሽ መስጠት ላይ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እንደሚገልጹ ተጠቁሟል። ኢጋድ በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የጋራ ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመልክቷል። ዜጎች ህጋዊ አማራጮችን እንዲከተሉና የኢኮኖሚ ፈተናን ጨምሮ ለሌሎች ገፊ ምክንያቶች ዘላቂ መፍትሄ መስጠት በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ ገልጿል። ስብሰባው ጥቅምት 10 እና 11 በባለሙያዎች፣ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚኒስትሮች ደረጃ ይካሄዳል።
የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በቁርጠኝነት ሊተገብሩ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት
Oct 19, 2025 436
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) አፈጻጸም ውጤታማነት ለማሳደግ በትኩረት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብስባ ከጥቅምት 11 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች እና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገም እና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስ እና ዘላቂ የውሃና ተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩ ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚከናውን ኢዜአ ከህብረቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
የብዙዎች ቤት…
Oct 27, 2025 228
እስካሁን በተደረገ የጥናት ውጤት መሠረት ከ81 በላይ የአጥቢ እንስሣት፣ ከ450 በላይ የአዕዋፍ እና ከ400 በላይ የእፅዋት ዝርያዎች መኖሪያ ነው። ከእነዚህ መካከል አምስቱ የአዕዋፍ ዝርያዎች በዚህ ሥፍራ ብቻ ይገኛሉ፤ ከአምስቱ መካከል በተለይም የአንዷ ዝርያ ዓለም አቀፍ የዘርፉ ተመራማሪዎችንና ጎብኚዎች ቀልብ መሳቡ ይጠቀሳል። ከአካባቢው ተፈጥሯዊ አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ጋር መጣጣም የቻሉ የቆላ እፅዋት (ዛፎች) በምቾት በስፋት እንደሚገኙበትም ይገለጻል። የተመሠረተው በ1958 ዓ.ም ሲሆን፤ ስፉቱም 591 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ነው፤ በቁጥርም ሆነ በሥብጥር የብዙዎች መኖሪያ የሆነው ይህ ሥፍራ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ይሰኛል። መንግሥት በሰጠው ትኩረት ከነበረው በተሻለ ሁኔታ እንስሣቱም ሆኑ እፅዋቱ እየኖሩ ነው፤ ከሕገ ወጥ ድርጊትም እንዲጠበቁ ማድረግ መቻሉን የፓርኩ ኃላፊ አደም መሐመድ ለኢዜአ አረጋግጠዋል። በፓርኩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁንም ለ247 ወገኖች ቋሚ እና ለ2 ሺህ 535 ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ባሳለፍነው ዓመትም በ1 ሺህ 751 የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች እንደተጎበኘ ኃላፊው ገልጸዋል።
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 708
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል። ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው። የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው። ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል። ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 685
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም። በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል። የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል። በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል። በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል። በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 896
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1514
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2002
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2845
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2966
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 804
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 583
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6423
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4900
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የዳሰነቾች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ''
Oct 30, 2025 300
የዳሰነች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ'' (በጣፋጩ ሰለሞን ከጂንካ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ዳሰነቾች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በአብሮነት ተጎዳኝተው ይኖራሉ። የብሔረሰቡ አባላት ዋነኛ መተዳደሪያ ከብት እርባታ ሲሆን፤ ከከብት እርባታው ጐን ለጐን በዝቅተኛ ደረጃ በግብርናና በዓሳ ማስገር ስራ ይተዳደራሉ፡፡ ዳሰነቾች በሰሜን ከሐመር፣ በደቡብ ከኬኒያ፣ በምስራቅ ከቦረና በስተ ምዕራብ ደግሞ ከኛንጋቶም ማህበረሰብ ተጎራብተው ይኖራሉ። ዳሰነቾች ከኩሽቲክ የቋንቋ ነገድ የሚመዘዝ ''አፍ ዳሰነች'' የተሰኘ የመግባቢያ ቋንቋም አላቸው። ዳሰነቾች የተለየ የአለባበስ፣ የአጋጌጥ፣ የቤት አሰራር እና የባህላዊ የሙዚቃ ስልተ ምትን ጨምሮ አስደማሚ ባህሎች እና ማራኪ የመልክዓ ምድር አቀማመጥን የታደሉ ናቸው። ዳሰነቾች ከሚታወቁባቸው አስደማሚ ባህሎች ውስጥ አንዱ የሆነው አለመግባባቶችን በውይይት የሚፈቱበት የ''ጀለባ''ስርዓት ተጠቃሽ ነው። ይህ ስርዓት ግጭቱ ቂምና ቁርሾ በማይሻገርበት መልኩ በዘላቂነት የማስወገድ አቅም ያለው ሲሆን የማይናወጥ ሰላምና ወንድማዊ ትስስር እንዲጠናከርም ሚናው የጎላ ነው። ዕሴቱ የዳሰነቾች የአኗኗር ቁመና የሚለካበትና የሚመዘንበት መጻኢንም የሚተለምበትም ጭምር ነው። ስለሆነም በዳሰነቾች ዘንድ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል ነው የሚባለው። የባህሉ ተመራማሪ ሊዮን አርሎት 'ጀለባ'' የተሰኘው ባህላዊ ዳኝነት ከአካባቢው ሰላም አልፎ ለቀጠናው ወንድማማችነት መጠናከር ትልቅ ሚና ያለው የፍትህ ስርዓት መሆኑን ያነሳሉ። በ''በጀለባ'' ስርዓት ባህላዊ የዳኝነት አሰጣጥ እርከኖች እንዳሉ ጠቅሰው፥ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ ''ኖሞ'' የተሰኙ ሽማግሌዎች ወደ ስፍራው በማቅናት የግጭቱን መንስኤ በማጣራት ''ቶሎል'' ለተሰኙ ሌሎች ሽማግሌዎች የሚያሳውቁበት አሰራርም አላቸው። እንደ ግጭቱ ቅለትና ክብደት ''ቶሎል'' በተሰኙ ሽማግሌዎች ተለይቶ ቀለል ያለው ''ካባና'' በተሰኙ ዳኞች ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን፥ ጉዳዩ ከበድ ያለ ከሆነ ደግሞ የመጨረሻው ውሳኔ ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች ይሰጣል። ከነፍስ ማጥፋት በስተቀር ሁሉም ውሳኔዎች ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች እልባት ያገኛሉ። የነፍስ ማጥፋት ወንጀል ሲከሰት ግን ጉዳዩን ለመንግሥት አሳልፎ በመስጠት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያገኝ ይደረጋል ። ነፍስ ያጠፋው ሰው የእርምት ጊዜውን አጠናቆ ማህበረሰቡን ለመቀላቀል ሲወስን ባህላዊ የዕርቅ ስነ-ስርዓት ተዘጋጅቶ በዳይና ተበዳይ ይቅር የሚባባሉበትም ስርዓት እንዳለ የባህሉ ተመራማሪ ይናገራሉ። በዳሰነቾች ባህል ልዩነቶች ሰላማዊ በሆነ መንገድ በዘላቂነት መንገድ የመፍታት ዘመናትን የተሻገረ ድንቅ ዕሴት መኖሩን የሚያነሱት የብሔረሰቡ አባል አሸቴ ነካሲያ፤ “በዳሰነች ብሔረሰብ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል'' ይላሉ። በዳሰነቾች አለመግባባቶች በውይይት የሚፈቱበት ስርዓት እንዳለ ጠቅሰው፥ ''ናብ'' በተሰኘው የዳኝነት ስፍራ አለመግባባቶች ውለው ሳያድሩ እልባት ያገኛሉ ብለዋል። ሌላው የብሔረሰቡ አባል ሎቶያቡስ ሎኪሰሬሬ በበኩላቸው የባህል መሪዎች የተጣላን ማስታረቅ፣ ትውልዱን የመግራትና በስነ-ምግባር የማነፅ ኃላፊነት እንዳላቸው ጠቅሰዋል። ''ማንም ሰው ከባህል መሪዎች ትዕዛዝ አያፈነግጥም'' የሚሉት አቶ ሎቶያቡስ፥ ሁሉም እርስ በእርስ በመከባበር እና ችግሮች ሲኖሩ በውይይት በመፍታት አብሮነቱን ያጠናክራል ብለዋል። ወጣቱ ለባህል መሪዎች ታዛዥ ነው የሚሉት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ የብሔረሰቡ አባል ሎሲያ ሎብቻ ወጣቶች ለአካባቢው ሰላም ዘብ እንዲቆሙ፣ ከአጎራባች ህዝቦች ጋር በፍቅር እንዲኖሩ በማስተማር ወጣቱን በስነ-ምግባር የማነፅ ስራ እንደሚሰሩም ተናግረዋል። የዳሰነች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ በበኩላቸው የዳሰነች ህዝብ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ከወረዳው አልፎ ለቀጠናው ሰላም ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። የብሔረሰቡ ባህላዊ የሽምግልና ስርዓት ትውልዱን በመግራት በስነ- ምግባር የታነፀ ዜጋ እንዲፈጠር እንዳደረገም አስረድተዋል። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የሶሻል አንትሮፖሎጂ መምህርና ተመራማሪ አጎናፍር ሰለሞን፤ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓቶች ለዘመናዊው የፍትህ ስርዓት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል ብለዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች ቅጣት በመጣል ጥፋተኝነት እንዲሰማ የሚያደርጉ ሳይሆኑ፤ እውነተኛ ይቅርታን የሚያሰፍኑና ለአብሮነት የሚበጁ ዕንቁ ባህሎች እንደሆኑም አብራርተዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹ በግለሰብ ተጠቃሚነት ላይ ሳይሆን በማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት የሚያደርጉ በመሆናቸው ከዘመናዊው የፍትህ ስርዓት በይበልጥ ለአብሮነት መጠናከር አስተዋጽኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹም ለሀገራዊ መግባባት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ፥ እሴቶቹ ተጠብቀው፣ ለምተውና ጎልብተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት እንደሚገባም መክረዋል። ሀገራችን ቂምና ቁርሾን የወለዱ ያለመግባባቶች በዘላቂነት በሰለጠነና ሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ሁሉንም ያሳተፈ ስራ እየሰራች እንደሆነ ያነሱት መምህርና ተመራማሪው አጎናፍር ሰለሞን ዕሴቶቹ በማህበረሰቡ ዘንድ ካላቸው ተቀባይነት እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ሂደቱን ከማገዝ አንጻር ጉልህ ሚና ስለሚኖራቸው መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
''ቦር ተራራ'' የየሞች የፈውስ ምድር
Oct 27, 2025 289
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) የም ዞን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ይገኛል። በዞኑ የቦር ተራራ ዋነኛው የመድኃኒት እጽዋት መገኛ እና ምንጭ በመሆኑ የሞች በየዓመቱ ጥቅምት ወርን ጠብቀው በ17ኛው ቀን ከዚህ ተራራ በህብር ሆነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስነ-ስርዓት ያካሂዳሉ፤ ይሰባስባሉም ። የቀደምት የየም አባቶችና እናቶችን በማሳተፍ የሚከወነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ከባህር ጠለል በላይ 2 ሺህ 939 ሜትር ከፍታ ላይ በሚገኘው ቦር ተራራ ላይ ነው። በዚህ ተራራ ላይ በየዓመቱ ጥቅምት 17 ቀን የሞች ለዓመት የሚያገለግላቸውን የመድኃኒት እጽዋት ይለቅማሉ። ተግባሩንም አዋቂዎች በጋራ ሰብሰብ ብለው ለመድኃኒት የሚውለውን ቅጠል በጥሰው፣ ስር ምሰው፣ አስሰውና መርጠው ይሰበስባሉ። ይህም የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስርዓት "ሳሞ ኤታ" ተብሎ ይጠራል ። አያምጣውና ህመም ሲከሰት ታማሚውን ሰው ወይም እንስሳን ከበሽታው ለመፈወስ የተዘጋጀው ባህላዊ መድሃኒት በባህላዊ ሃኪም ትዕዛዝ መሰረት በህመሙ ልክ ይታዘዝለታል። መድሃኒቱን ለመጠቀምም የጠቢባን አባቶችን ፈለግ ተከትሎ መፈፀም የግድ ይላል። የሞች አጅግ አስገራሚ እና አስደናቂ የሆኑ የበርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤት ናቸው ካስባሏቸው እሴቶች መካከል ይህ ለየት ያለው ክዋኔያቸው አንዱ ነው፡፡ አባቶች ታዳጊና ወጣቶችን አስከትለው ወደ ቦር ተራራ በመውጣት የሚፈፅሙት ባህላዊ ክዋኔ በመሆኑም ከትውልድ ወደ ትውልድ ቅብብሎሹን ጠብቆ እስከ አሁን እንዲዘልቅ እድርገውታል። በየሞች ዘንድ የባህላዊ መድኃኒት አዋቂዎች ከሚባሉት መካከል አንዱ አቶ ጌታቸው ሃይለማርያም፤ የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ልምድን የቀሰሙት ከአባታቸው መሆኑን በመግለፅ አያታቸው ከቅድመ አያቶቻቸው በመውረስ እዚህ እንዳደረሱት ይናገራሉ። የቦር ተራራ ለመድሃኒት ዕፅዋት ለቀማው የተመረጠበትን ምክንያት ሲያስረዱም ቦታው ተራራ በመሆኑ ማንም ያልደረሰባቸው የተለያዩ እፅዋትን ለማግኘት አመቺ ከመሆኑ ጋር ያያይዙታል። በሌላም በኩል ጠዋት ፀሐይ ስትወጣ መጀመሪያ የምታገኘው ተራራውን በመሆኑና ክረምቱ አልፎ ጥቅምት ሲገባ የተለያዩ ቅጠላ ቅጠሎችን በብዛት እና በዓይነት ለማግኘት ተመራጭ ወቅት መሆኑም ቦታው የተመረጠበት ሌላኛው ምክንያት ነው ብለዋል። በጥቅምት 17 ለመድኃኒትነት የሚያገለግለው ዕፅዋት ቅጠልም በየፈርጁ ተለቅሞ እና ተቀምሞ ይቀመጣል ሲሉም አስረድተዋል። የተዘጋጀው ባህላዊ መድኃኒትም ለሰው ልጆችና ለቤት እንስሳት ያገለግላል ሲሉም አስረድተዋል፡፡ ይኸው በዚህ ቀን የተለቀመው የመድኃኒት ዕፅዋት ከዚህኛው ጥቅምት 17 እስከሚቀጥለው ዓመት ጥቅምት 17 ድረስ እንደሚያገለግልም አቶ ጌታቸው አስረድተዋል፡፡ የባህል መድኃኒት ሰብሳቢዎች እና ተጠቃሚዎች ጊዜውን ጠብቀው ከተለያዩ ቦታዎች ወደ ቦር ተራራ እንደሚመጡ የሚገልጹት የባህል መድኃኒት አዋቂው ዛሬ ዛሬ እሳቸውን ጨምሮ መድኃኒት ቤቶችን በመክፈት ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ የባህል መድኃኒቶችን በመሸጥ ኑሯቸውን እየመሩ የሚገኙ አያሌ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉም ይናገራሉ። ሌላኛው የባህል መድኃኒት አዋቂው አቶ ወልደመስቀል ጆርጋ በበኩላቸው በየሞች ዘንድ የተዘጋጀው የመድኃኒት ዕፅዋት ጥቅም ላይ የሚውለው ህመም ሲያጋጥም ብቻ ሳይሆን በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል መሆኑን ጠቁመው መድኃኒቶቹም ብቻቸውን እንዲሁም ከምግብ ጋር በመመገብ ለጥቅም እንደሚውሉም አንስተዋል። የየም ምድር የበርካታ የመድኃኒት ዕፅዋቶች መገኛ አካባቢ " የፈውስ ምድር " ነው የሚሉት ደግሞ በየም ባህላዊ መድኃኒት ዙሪያ ጥናት ያደረጉት በጅማ ዩኒቨርሲቲ የፎክሎር መምህር እና ተመራማሪ ለማ ንጋቱ (ዶ/ር) ናቸው። ከየሞች አያሌ የባህል ዕሴቶች መካከል የባህል መድኃኒት ለቀማና ቅመማ አንዱና ዋነኛው የሀገር በቀል እውቀት ማሳያ መሆኑን ገልፀው የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ስነ-ስርዓቱ ከጥንት ጀምሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ዛሬ ላይ የደረሰ እንደሆነም ያስረዳሉ፡፡ ማህበረሰቡ የራሱንም ሆነ የእንስሳትን ጤና የመጠበቅ የቆየ ባህል ያለው መሆኑን በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው የባህላዊ መድኃኒት ለቀማው ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚሳተፉበት ዓመታዊ ክዋኔ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ሌላው ገራሚው ነገር ይላሉ አጥኚው ታላላቆች ታናናሾቻቸውን አስከትለው የለቀማ ሂደቱን የሚያስረዱበት መንገድ ደግሞ ስርዓቱ ለመጪው ትውልድ እንዲተላለፍ የሚያስችል ትውልድ ተሻጋሪ የሀገር በቀል እውቀት ሽግግር ስርዓት ማሳያ እንደሆነም ነው የገለጹት። በዚህም ሂደት የሚነገሩ ስነ-ቃሎች መሞጋገስ፣ ጭፈራና ደስታ ይስተናገድባቸዋል። ይህም ማህበራዊ ትስስርን ይበልጥ የሚጠናክሩበትን ሁነት የሚፈጥር ስርዓት ነው። የየም ዞን ባህል እና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ሞጋ በበኩላቸው የቦር ተራራ የመጀመሪያውን የማለዳ የፀሐይ ጎህ የሚፈነጥቅበት የንጋት ብርሃን ቀድሞ የሚያገኝ በመሆኑ፥ በዚህ አካባቢ የሚገኙ እጽዋት በሽታን የመከላከልና ፈዋሽነታቸው ከፍተኛ ነው ተብሎ ስለሚታመን ለዚህ ክዋኔ ቦታው መመረጡን ነው የሚገልፁት። ለዚህም ነው የሞች ይህንን ስፍራ ከሌሎች ቦታዎች አስበልጠው የሚወዱት፤ በየዓመቱም ጥቅምት 17 ቀን ወደ እዚህ ስፍራ በማቅናት ለዓመት ፍጆታ የሚያገለግላቸውን መድኃኒትም ይሰበስቡበታል ብለዋል። ጥቅምት 17 በየም ዘንድ ለየት የሚያደርገው ሌላው የመድሃኒት ዕፅዋት ለመልቀም እና ለመጠቀም ብቻ ሳይሆን የለቀማውን ትዕይንት ለመመልከት የሚመጡ ቱሪስቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸው ሌላው ትልቁ ትሩፋት ነው ይላሉ። የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማው ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት በመሆኑ፥ ለአብሮነት እና ሃገር በቀል እውቀት ለመቅሰም ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ነው አቶ መስፍን የገለፁት።