ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በደብረ ማርቆስ ከተማ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Feb 27, 2026 7
ደብረ ማርቆስ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በደብረ ማርቆስ ከተማ ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተመላከተ። በከተማዋ ወቅታዊ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ላይ ያተኮረ የወጣቶች ውይይት ተካሂዷል። በአማራ ክልል በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የወጣቶች ተጠቃሚነት እያደገ መጥቷል የከተማ አስተዳደሩ ስራና ክህሎት መምሪያ ምክትል ሃላፊ ዘሪሁን ደገፍ እንዳሉት፤ በከተማዋ ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው። በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ከ18 ሺ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ እስካሁን ባለው ሂደት ከ12 ሺ በላይ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል። ከተማ አስተዳደሩ ለወጣቶች የመስሪያና የመሸጫ ሼዶችን ከማመቻቸት ባለፈ ከ17 ሚሊየን ብር በላይ ብድር ማመቻቸቱንም ተናግረዋል። የከተማዋን ሁለንተናዊ ልማትና ዕድገት ለማረጋገጥ ወጣቶች የአካበቢያቸውን ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የከተማ አስተዳደሩ የሕዝብ ግንኙነትና አደረጃጀት ኃላፊ መልካሙ ሽባባው ፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት የነበረው የጸጥታ ችግር በኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ዘርፎች ላይ ጫና ማሳደሩን አስታውሰው አሁን ግን መሻሻሎች መኖራቸውን ገልጸዋል። ወጣቱ በከተማዋ የተገኘውን ሰላም ለማደናቀፍ የሚሞክሩ አካላትን በንቃት በመከላከል ተጠቃሚነቱን ሊያሳድግ ይገባል ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ጫኔ ታደለ፤ በንብ ማነብ ዘርፍ ተሰማርቶ ውጤታማ እየሆነ መሆኑን ጠቅሶ የአካባቢውን ሰላም ለመጠበቅ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል። ወጣት ምህረት መልካም በበኩሏ ሰርቶ መለወጥ የሚቻለው ሰላም ሲኖር በመሆኑ መንግስት ሰላምን ለማስፈን በሚያደርገው ጥረት ውስጥ የድርሻዋን እንደምትወጣ ተናግራለች።
የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ለሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን የኢፋ ቦሩ 2ኛ ጀረጃ ትምህርት ቤት ስጦታ አበረከተ
Feb 27, 2026 27
አምቦ ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦የቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጽህፈት ቤት በአምቦ ከተማ አስተዳደር ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን በተወለዱበት ኢላሞ ጎረምቲ ወረዳ ለሚገኘው ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን የኢፋ ቦሩ 2ኛ ጀረጃ ትምህርት ቤት ስጦታ አበረከተ። በሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን የጥበብ ስራዎች ውስጥ ትውልዱ ራሱን በማየት የሀገሩን አርት ለማሳደግ መትጋት አለበት ስጦታዎቹም የተለያዩ ኮምፒዩተሮች፣ ፕሪንተሮች፣ መፅሀፍቶች፣ የሚኒ ሚዲያ ቁሳቁሶች፣ የሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ፣ የህክምና መሳሪያዎች እና ሌሎች ለመማር ማስተማር የሚያገለግሉ ግብአቶች ነው። የቀዳማዊት እመቤት ፅህፈት ቤት ይህን ስጦታ ያበረከተው በአምቦ ከተማ የሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን 20ኛ አመት የዕረፍት መታሰቢያ ፕሮግራም ላይ ነው። ዛሬ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን የሚያስተምረው ትምህርት ቤቱ የተገነባው በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጽህፈት ቤት በ2015 ዓ.ም ሲሆን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመፅሀፍ ሽያጭ በተገኘ ገቢ ነው። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ)፤ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልእክት በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ስም ትምህርት ቤቱ መገንባቱ ትልቅ የታሪክ አሻራ መሆኑን አንስተው የአሁኑ ትውልድም ለጥበብ ስራዎች የሀገሩን ጥበብ ለማሳደግ መትጋት አለበት ብለዋል። የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ትምህርት ቤቱን ከማስገንባት ባለፈ፣ ለተማሪዎች የመማር ማስተማር ሂደት ግብዓት የሚሆኑ ልዩ ልዩ ድጋፎችን ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ለትምህርት ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ ላፕቶፖች፣ ፕሪንተሮችና ሌሎች የትምህርት መርጃ መሣሪያዎችን ጨምሮ በጠቅላላው 8 ሚሊዮን ብር የሚገመት ቁሳቁስ በስጦታ መልክ መበርከቱን ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ ከተገኙት አርቲስቶች መካከል አርቲስት አበበ ባልቻ፤ የሎሬቱ የጥበብ ሥራዎች በርካታ አርቲስቶችን በማፍራት በሀገራችን የጥበብ እድገት ውስጥ የማይረሳ አሻራ አኑረዋል ብሏል። የሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህንን አርአያነት በመውሰድ፣ የሀገራችንን ጥበብ አሁን ካለበት ለማሳደግ መስራት ይጠበቅብናል ብሏል። በመሆኑም በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጽህፈት ቤት በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ስም የተሰየመው የኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግሯል። አርቲስት ተፈሪ ዓለሙ፤ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ከኢትዮጵያ አልፎ የአፍሪካ የጥበብ እድገት በዓለም መድረክ እንዲታይ ያደረገ ታላቅ ባለውለታ መሆኑን ገልጿል። በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ስም ለተሰየመው የኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ በቀጣይ ሌሎች አርቲስቶችን በማስተባበር ድጋፍ እናደርጋለን በማለት አርቲስቶቹ ቃል ገብተዋል። የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ ደራራ ከተማ፤ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን የሀገራችንን አርት ለዓለም ያስተዋወቁ ድንቅ የሀገር ባለውለታ በመሆናቸው ታላቅ ክብር የሚገባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጽህፈት ቤት በሎሬቱ ስም ትምህርት ቤቱ በመገንባቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያን ክብርና ሉዓላዊነት በማስጠበቅ የአባቶቹን የዓድዋ ጀግንነት ታሪክ እያስቀጠለ ነው
Feb 27, 2026 24
ሰቆጣ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያን ክብርና ሉአላዊነት በማስጠበቅ የአባቶቹን የዓድዋ ጀግንነት ታሪክ እያስቀጠለ መሆኑን የሰራዊቱ አባላት ገለጹ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የመከላከያ ሠራዊት አመራሮችና አባላት የዓድዋን የጀግንነት ታሪክ በመድገም የሀገርን አንድነትና ዳር ድንበር የማስጠበቅ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም የተገኘ የአንድነት ውጤት ነው በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የሚገኙ የሠራዊቱ አባላት ለሀገር ሉዓላዊነትና ቀጣይነት ላለው ዕድገት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የዓድዋ ድል ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመውረር የነበረውን ሕልም ያከሸፈ ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ጮራን የፈነጠቀ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው። ከሰራዊቱ አመራሮች መካከል ሻለቃ ተክላይ አማረ፤ የዓድዋ ድል የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና የሕዝቦች አንድነት በተግባር የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። ሠራዊቱ ዛሬም የአባቶቹን አርበኝነት በመውረስ የሕዳሴው ግድብን በመገንባት የዳግማዊ ዓድዋን ታሪክ በደማቁ ጽፏል ብለዋል። የዓድዋ ድል የውጭ ወራሪን ብቻ ሳይሆን የውስጥ ባንዳዎች ተልዕኮ የከሸፈበት መሆኑን ጠቅሰው፣ ሠራዊቱ በአሁን ጊዜ የሀገርን ሉዓላዊነት ለመፈታተን የሚሞክሩ የውስጥና የውጭ ኃይሎችን ድል የማድረግ ብቁ ቁመና ላይ ነው ብለዋል። የ204ኛ ኮር ሻምበል አዛዥ መቶ አለቃ እንድሪስ ጀማል፤ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ከቆሙ ለዓለም የሚተርፍ ታሪክ መስራት እንደሚችሉ ዓድዋ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። ሠራዊቱ ከጀግና አባቶች የተረከባትን ሀገር ዳር ድንበሯን አስጠብቆ ለተተኪው ትውልድ ለማስረከብና የተሰጠውን ግዳጅ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። ምክትል አስር አለቃ አጥቃቸው ሙሉዬ፤ ጀግኖች አርበኞች ዘመናዊ መሣሪያ የታጠቀውን ጠላት በሀገር ፍቅር ስሜት እንዳሸነፉት ሁሉ ዛሬም ሠራዊቱ ያንን ጽናት በመላበስ ማንኛውንም ተልዕኮ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ ነው ብለዋል። ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ልማት በትጋት የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት ነው ብለዋል። 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል ''ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ'' በሚል ሀሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል።
በሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን የጥበብ ስራዎች ውስጥ ትውልዱ ራሱን በማየት የሀገሩን አርት ለማሳደግ መትጋት አለበት
Feb 27, 2026 42
አምቦ ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ በሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን የጥበብ ስራዎች ውስጥ ትውልዱ ራሱን በማየት የሀገሩን አርት ለማሳደግ መትጋት አለበት ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ) ገለጹ። ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን 20ኛ ዓመት ህልፈተ ህይወት መርሃ ግብር መነሻውን በአዲስ አበባ ራስ መኮንን ድልድይ (70 ደረጃ) ከሚገኘው የሎሬቱ መታሰቢያ ሐውልት ጋር በማድረግ ወደ ሎሬቱ ትውልድ ከተማ አምቦ በማቅናት በተለያዩ ኹነቶች ተከብሯል። በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የኪነ-ጥበብና ስነ-ጥበብ ፈጠራ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ) በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ መርሃ ግብሩ የተዘጋጀው የሎሬቱን የጥበብ ትሩፋትና በጎ አሻራ ለወጣቱ ትውልድ ለማስተላለፍ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም የአሁኑ ትውልድ ራሱን በሎሬቱ የጥበብ ስራዎች ውስጥ በማየት የሀገሩን አርት ለማሳደግ ጠንክሮ መስራት አለበት ብለዋል። ለዚህም በየዓመቱ የሎሬት ፀጋዬን የአርት ስራዎች የሚዘክርና የሚያሳዩ ስራዎችን በቋሚነት ለመስራት ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ማቀዱንም ጠቁመዋል። የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ ደራራ ከተማ በበኩላቸው፤ ሎሬቱ የሀገራችንን አርት ለዓለም ያስተዋወቁ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ቢሮው መሰል የጥበብ ሰዎችን ለማፍራት የሚያስቸሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመው ይህንንም ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት አርቲስቶችም የሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህንን አርአያነት በመውሰድ፣ የሀገራችንን ጥበብ አሁን ካለበት ለማሳደግ ተባብረው እንደሚሰሩም ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ የተገኘው አርቲስት አበበ ባልቻ እንደገለፀው፤ የሎሬቱ የጥበብ ሥራዎች በርካታ አርቲስቶችን በማፍራት በሀገራችን የጥበብ እድገት ውስጥ የማይረሳ አሻራ አኑረዋል። አርቲስቱ አክሎም በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ስም ለተሰየመው የኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ሌሎች አርቲስቶችን በማስተባበር በየዓመቱ በመምጣት አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርጋለን ብሏል። ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን የኢትዮጵያን ጥበብ ከማሳደግ ባለፈ የአፍሪካ የጥበብ እድገት በዓለም መድረክ እንዲታይ ያደረገ መሆኑን የገለፀው ደግሞ አርቲስት ተፈሪ አለሙ ነው። ሀገራችን ኢትዮጵያን እንድንወድ ያደረገ ታላቅ አርቲስት ነው ሲልም ገልጿል።
ምድረ ገነት ሽሬ እና ሀዲያ ሆሳዕና ድል ቀንቷቸዋል
Feb 27, 2026 44
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ጨዋታዎች በመካሄድ ላይ ናቸው። በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መቻል እና ሃዋሳ ከተማ ነጥብ ተጋሩ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ምድረገነት ሽሬ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 1 አሸንፏል። ዳንኤል ዳርጌ እና ደሳለኝ ከተማው የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ደሳለኝ ከተማው በ96ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል ለቡድኑ ወሳኝ ሶስት አስገኝታለች። ናትናኤል ዳንኤል ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቸኛውን ግብ አስቆጥሯል። ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ምድረ ገነት ሽሬ በ26 ነጥብ ደረጃውን ከ15ኛ ወደ 10ኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ስድስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ24 ነጥብ ከነበረበት 11ኛ ደረጃ ወደ 13ኛ ዝቅ ብሏል። በሌላኛው መርሐ ግብር ሀዲያ ሆሳዕና ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 አሸንፏል።ደስታ ዋሚሾ በ79ኛው ደቂቃ ግቧን አስቆጥሯል። ወደ አሸናፊነት መንገድ የተመለሰው ሀዲያ ሆሳዕና በ27 ነጥብ ደረጃውን ከ13ኛ ወደ 9ኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ ሰባተኛ ድሉን አሳክቷል። በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ28 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ስድስት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም።
ፖለቲካ
በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Feb 27, 2026 53
ሆሳዕና፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች መመዝገባቸውን የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ባደረጋቸው ጥረቶች የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ያስቀጥላል በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲ ምህዳርን በማጠናከር አዲሷን ኢትዮጵያን ለመገንባት ሚናው የጎላ መሆኑም ተመላክቷል። ብልጽግና ፓርቲ የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱ የሆነውን (የስንዴ ነዶ) እና ማኒፌስቶ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ለህዝብና ለአባላቱ አስተዋውቋል፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ በዚህ ወቅት እንዳሉት ብልጽግና ፓርቲ በድህነት ቅነሳ ላይ ባከናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል። ፓርቲው የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሀሳቦችን በማቅረብና ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ጭምር በትብብር በመስራት ስኬት እያስመዘገበ መሆኑንም አስታውሰዋል፡፡ በዞኑ በሰላም ግንባታ፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በጤናና በትምህርት ዘርፍ በተከናወኑ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ ወጤት እየተመዘገበ ስለመሆኑም ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከድህነት በመውጣት በምግብ ራስን ለመቻል በተተገበሩ የሌማት ትሩፋት መርሀግብርና ሌሎች ኢኒሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት መምጣቱንም ጠቁመዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በፓርቲው መሪነት በተለያዩ ዘርፎች በተከናወኑ የልማት ሥራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ነው ያስታወቁት። በዞኑ በልማትና በመልካም አስተዳደር በተሰሩ ሥራዎች እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የፓርቲው አመራሮችና አባላት የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል። በብልጽግና ፓርቲ የሀዲያ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ግዛው በበኩላቸው፤ የለውጡ መንግሥት የፖለቲካ ስልጣን ቅቡልነት በህዝብ ድምፅ ብቻ እንዲወሰን ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በሀገሪቱ የተጀመረውን የዴሞክራሲ ምህዳር በማጠናከር ለአዲሷ ኢትዮጵያ ግንባታ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የፓርቲው አባላት ተሳትፈዋል፡፡
ምርጫው ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው- ፓርቲዎች
Feb 27, 2026 53
ደሴ ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድና ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክሮች ለሀገርና ህዝብ በሚጠቅሙ የፖሊሲ አጀንዳዎች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል በአማራ ክልል ደሴ ከተማና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በደሴ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂደዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢና በኢዜማ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ ሻምበል ደምሌ ተረፈ፤ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርአት መዳበርና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ምርጫ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ የጋራ ምክር ቤቱ የዘንድሮው ምርጫ በሃሳብ የበላይነት በመፎካከር ሀገርን አሸናፊ የሚያደርግ እንዲሆን ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድና ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው ሲሉም ተናግረዋል። የዛሬው ውይይት ዋነኛ ዓላማም በምርጫው ሂደት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በጋራ በመፍታት ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ማካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢና በብልጽግና ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አለማየሁ፤ ለምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የጋራ ምክር ቤቱ አባላት በቅንጅት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። ለምርጫው ተወዳዳሪ እጩዎችንና ታዛቢዎችን መመልመላቸውን ጠቁመው በቅስቀሳ ወቅት ከጠብ አጫሪነትና ጥላቻ ንግግሮች በመራቅ መራጩ የጠራ ግንዛቤ አግኝቶ እንዲወስን ማድረግ የሁላችንም ሃላፊነት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባልና የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ተወካይ አቶ ያለው አሸብር፤ በሀገር ዘላቂ ሰላም፣ ጥቅምና ልማት ፓርቲያችን አይደራደርም ብለዋል። በወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ መሀመድ የሱፍ፤ በቅደመ ምርጫ፣ በምርጫና በድህረ ምርጫ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማስተካከል የዛሬው ምክክር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በሁሉም ፓርቲዎች ዘንድ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማስተካከል የተሳካ ምርጫ ለማካሄድ የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት ያስችላል
Feb 27, 2026 55
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት እንደሚያስችል የኢፌዲሪ የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በክልሎች፣ በከተማ አስተዳደሮችና በውጭ ዓለማት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የአጀንዳ ማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ አካሂዷል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን በስኬታማነት ለማስቀጠል የሁሉም አካላት ሚናና ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድም የአጀንዳ ቀረፃና የግብዓት ማሰባሰብ የዝግጅት ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል። በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ በ1ኛ ዓመት አስቸኳይ ጉባኤም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የስራ ዘመን ለሁለተኛ ጊዜ ለሚቀጥሉት ስምንት ወራት ተራዝሟል። የኢፌዲሪ የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ኃይለየሱስ ታዬ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ብሔራዊ መግባባት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት፣ ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም በሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም ዙሪያ የዜጎችን ግንዛቤ በማሻሻል የዳበረ የዴሞክራሲ ሥርዓትን ለመገንባት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ተግባራትም የዜጎችን ግንዛቤ በማሳደግ ሕብረብሔራዊ አንድነትን እያጎለበቱ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በቀጣይም በክልሎች ጭምር የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል። የዜጎችን የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም ሥርዓት ግንዛቤ ለማጎልበትም በተለያዩ የህዝብና የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች መልዕክቶችና ትምህርቶች እየተላለፉ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክርም መግባባት ባልተደረሰባቸው ዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር የጋራ መግባባትን ለመፍጠር መሠረት የሚጥል መሆኑን ተናግረዋል። ለኢትዮጵያውያንም በሀገራዊ ምክክሩ የተመቻቸውን ዕድል በመጠቀም ብሔራዊ መግባባትን መፍጠርና ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት እንደሚያስችል አስገንዝበዋል። የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከልም ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት በዕውቀት ላይ የተመሰረቱ አጋዥ ሃሳቦችን በማፍለቅ እንደሚሰራ አንስተዋል።
በምርጫው የሀሳብ ልዕልና እንዲያሸንፍ ስልጡን የፖለቲካ ባህል እንከተላለን - ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች
Feb 27, 2026 59
ጎንደር፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ በጠቅላላ ምርጫው የሀሳብ ልዕልና እንዲያሸንፍ ስልጡን የፖለቲካ ባህል በመከተል የድርሻቸውን እንደሚወጡ በጎንደርና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀሳብ የበላይነት የሚያሸንፍበት እንዲሆን የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል እንደሚከተሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ/ኢዜማ/የጎንደር ቅርንጫፍ ተወካይ ዝናወርቅ ታደለ እንዳሉት፣ ፓርቲያቸው ትብብርና ፉክክርን መርህ ያደረገ የምርጫ ውድድር ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቅቋል። የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል በማራመድና በሃሳብ ልዕልና ላይ የተመሰረተ ምርጫ በማካሄድ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ግንባታ ለይ አሻራ እንደሚያኖሩ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም በጠቅላላ ምርጫው በንቃት ለመሳተፍ የምርጫ ምልክታቸውንና ማኒፌስቷቸውን ለሕዝብ እያስተዋወቁ መሆኑን ተናግረዋል። የቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት ተገኑ ደረጀ በበኩላቸው ፓርቲያቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ሥነ ምግባር ደንቡን አክብሮ ለውድድር እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ጥቅምንና የህዝብን ክብር ባከበረ መልኩ የሕዝብ ድምፅ ለማግኘት የምረጡኝ ቅስቀሳ እያካሄዱ መሆኑን ጠቁመዋል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ሀሳብ ላይ የተመሰረተ ክርክር ማካሄድ የስልጡን ፓርቲዎች ተግባር መሆኑንም ተፎካካሪ ፓርቲዎቹ ገልጸዋል።
የብልጽግና ፓርቲ የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ባደረጋቸው ጥረቶች የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ያስቀጥላል
Feb 27, 2026 76
ወልቂጤ ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፡- የብልፅግና ፓርቲ ያሉትን ፀጋዎች ወደ ውጤት በመቀየር የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ባደረጋቸው ጥረቶች የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ተገለፀ። የብልፅግና ፓርቲ በጉራጌ ዞን ''ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር'' በሚል መሪ ሃሳብ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመወዳደሪያ ምልክት (የስንዴ ነዶ) እና የማኒፌስቶ የማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በወልቂጤ ከተማ አካሄዷል። በወቅቱም የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንዳሉት፣ የብልፅግና ፓርቲ የህዝብ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ባደረጋቸው ጥረቶች ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል። በተለይም በየአካባቢው የሚገኙ ፀጋዎች ወደ ውጤት እንዲቀየሩ በተደረጉ ጥረቶች ውጤቶች መመዝገባቸውን አውስተው ለአብነትም በግብርናው ዘርፍ በእርሻና በእንስሳት ልማት የተገኘውን ውጤት አንስተዋል። ዞኑ ያለውን አቅም ለመጠቀም በተደረገው ጥረት በእርሻ ኢንዱስትሪ በመሰረተ ልማትና በሌሎችም የልማት ስራዎች የዜጎችን ህይወት ያሻሻሉ ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰው ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ፓርቲው አበክሮ ይሰራል ብለዋል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ስርዓትን በመዘርጋት በስንዴ ልማትና በምግብ ራስን ለመቻል በተሰሩ ስራዎች እንዲሁም ውብና ፅዱ አካባቢን በመፍጠር ረገድ የሃገራችን ስም በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍ ብሎ እየተወሳ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፓርቲው እነዚህን የልማት ስኬቶች ለማስቀጠል ይተጋል ያሉት አቶ ላጫ አሰባሳቢ ትርክትን በመገንባትና ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ ህዝቡን የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል እንደ ሀገር የተወጠነውን የልማትና የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ በትጋት ይሰራል ብለዋል። በጉራጌ ዞን ያለውን ፀጋ በመጠቀም አርሶ አደሩን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ በማድረግ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና የስራ እድል ለመፍጠር ያስቻሉ ውጤቶች መገኘታቸውን ያነሱት ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ገብረመስቀል ናቸው። ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተደረገው ርብርብ ፍሬ እያፈራ መሆኑን በመጠቆም የህዝቡ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አንስተዋል። ፓርቲው ሰው ተኮር ለሆኑ የልማት ስራዎች በሰጠው ልዩ ትኩረት የዜጎችን ህይወት የቀየሩ ውጤቶች መገኘታቸውን አንስተው በየጊዜው በዞኑ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚሰራም ተናግረዋል። በመድረኩም የዞንና የከተማ አስተዳደሮች የስራ ሃላፊዎች፣ የወጣትና ሴቶች አደረጃጀቶች እና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዘርባጃን ፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ጋር ተወያዩ
Feb 27, 2026 70
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዘርባጃን ፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በአዘርባጃን ባደረጉት የመጀመሪያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ላደረጉላቸው ሞቅ ያለ እና የተከበረ አቀባበል ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በአቪዬሽን ዘርፍ፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮች እና በነፃ የንግድ ቀጣናዎች፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እና በአዘርባጃን አቻው መካከል በተደረጉ የኢኮኖሚ ትብብሮች ላይ በመመስረት የሀገራቱ አጋርነት በየጊዜው እያደገ መምጣቱን አመልክተዋል። የትብብር ዘርፎቹ ለሁለትዮሽ ግንኙነት መጠናከር መሠረት የጣሉ ሲሆን፣ ዛሬ ከፕሬዝዳንቱ ጋር በተደረገው ጥልቅ ውይይትም ግንኙነቱን እና ትብብሩን ይበልጥ ለማጠናከር እና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ከስምምነት ላይ መደረሱን ተናግረዋል። የሀገራቱ መሪዎች በዛሬው ዕለትም በመከላከያ እና በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ የመግባቢያ ሰነዶች ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ መገኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክሮች ለሀገርና ህዝብ በሚጠቅሙ የፖሊሲ አጀንዳዎች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል- ምሁራን
Feb 27, 2026 132
ሮቤ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፡-የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክሮች ለሀገርና ህዝብ በሚጠቅሙ የፖሊሲ አጀንዳዎች ላይ ያተኮሩ መሆን እንዳለባቸው የመደ ወላቡ ዩኒቨርስቲ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ፖሊሲዎቻቸውንና ስትራቴጂዎቻቸውን በመገናኛ ብዙኃን ለሕዝብ ማስተዋወቅ ጀምረዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ እንዲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጎላ ሚና እንዳላቸው አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገልጸዋል። ፓርቲዎች በምረጡኝ ቅስቀሳቸው ከጥላቻ ንግግሮች መራቅና ሀሳባቸውን በሰለጠነ መንገድ መግለጽ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ያግዛል ነው ያሉት ምሁራኑ። ፓርቲዎቹ የሚያቀርቧቸው አማራጭ ሀሳቦች ወደ መሬት ሊወርዱ የሚችሉና ሀገርን የሚያሻግሩ ሊሆኑ እንደሚገባም አንስተዋል። በዩኒቨርስቲው የስነ ዜጋና ሥነ-ምግባር ትምህርት መምህርና ተመራማሪ መቅደስ መስፍን እንዳሉት፣ ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅሰቀሳ ወቅት በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሳተፉ ይገባል። ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ጊዜ ለሀገር የሚበጅና ሊያሻግር የሚችል አማራጭ ፖሊሲና ስትራቴጂያቸውን በሰለጠነ መልኩ ሊያንጸባርቁ ይገባል ብለዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒነት እንዲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የምርጫ ሥነ-ምግባር ሕጉን ባከበረ መልኩ መንቀሳቀስ አለባቸው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነትና ሥነ- ተግባቦት ትምህርት መምህርና ተመራማሪ ኡመር መሐመድኑር ናቸው። በአሁን ጊዜ ፓርቲዎቹ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን አማራጮች አያደረጉት ያለው ክርክር በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው በመከባበር ላይ የተመሰረተ ሲሆን ነው ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የጂኦግራፊና አካባቢ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ ተስፋዬ ፈዬ (ረዳት ፕሮፌሰር) በበኩላቸው የፓርቲዎች ንግግርም ሆነ ተግባር ህዝብን ያከበረ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ጊዜ የሚያነሱት አማራጭ ሀሳብ ሕብረተሰቡ በቀላሉ ሊረዳው በሚችለው አግባብ መቅረብ እንዳለበትም አንስተዋል። በምርጫው ቅስቀሳና ክርክር ወቅት የሀገርን አንድነትና ሉአላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ንግግርም ሆነ ተግባር መፈጸም ተገቢ እንዳልሆነ በመረዳት ፓርቲዎች ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ነው ረዳት ፕሮፌሰሩ ያስገነዘቡት። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው
Feb 27, 2026 72
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እና ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የኢዜማ፣ የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የአብን ፓርቲ አመራሮች ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የሁሉንም አካላት ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ ምክትል መሪ አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን እንዳሉት፥ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የምርጫው ሂደት ስኬታማነት ወሳኝ ነው። በሂደቱም መራጩ ሕዝብ፣ ገዥው ፓርቲ፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ተቋማት፣ ምርጫ ቦርድና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የየራሳቸው የጋራና የተናጠል ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። ትልቁ ዓላማችን የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መሆን አለበት ያሉት አርክቴክት ዮሐንስ እያንዳንዱ ባለድርሻ አካልና ዜጋ ሕግን በማክበር ሀገራዊ ሚናውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀ-መንበር አበራ በቀለ በበኩላቸው የዘንድሮው ምርጫ ለኢትዮጵያ የተረጋጋ ፖለቲካዊና ዲሞክራሲያዊ ጉዞ ጠንካራ መሠረት የምናኖርበት ነው ብለዋል። በምርጫው የሚያሸንፍ ሐሳብ ይዘን እንቀርባለን ያሉት አቶ አበራ ምርጫው ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ የዲሞክራሲ ምዕራፍ የሚያሻግር ወሳኝ የታሪክ አጋጣሚ መሆኑን አስገንዝበዋል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) የሥራ አስፈጻሚ አባል የሱፍ ኢብራሂም፥ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሽግግር በዲሞክራሲያዊ ምርጫና በሀሳብ የበላይነት ብቻ መሆን እንዳለበት ፓርቲያቸው በጽኑ እንደሚያምን ገልጸዋል። ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እጅግ ሰፊ ዝግጅትን የሚጠይቅ መሆኑን ጠቅሰው ይህም ከማኒፌስቶ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ቀበሌ ድረስ አማራጭ ሐሳብን የማስተዋወቅ ሥራ እንደሚጠይቅ አስረድተዋል። ምርጫ የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ አካል በመሆኑ፥ ፓርቲያቸው ለሀገር ወሳኝ በሆነው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቀዋል።
ፖለቲካ
በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች ተመዝግበዋል
Feb 27, 2026 53
ሆሳዕና፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬቶች መመዝገባቸውን የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ባደረጋቸው ጥረቶች የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ያስቀጥላል በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲ ምህዳርን በማጠናከር አዲሷን ኢትዮጵያን ለመገንባት ሚናው የጎላ መሆኑም ተመላክቷል። ብልጽግና ፓርቲ የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ መወዳደሪያ ምልክቱ የሆነውን (የስንዴ ነዶ) እና ማኒፌስቶ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ለህዝብና ለአባላቱ አስተዋውቋል፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ በዚህ ወቅት እንዳሉት ብልጽግና ፓርቲ በድህነት ቅነሳ ላይ ባከናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል። ፓርቲው የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሀሳቦችን በማቅረብና ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ጭምር በትብብር በመስራት ስኬት እያስመዘገበ መሆኑንም አስታውሰዋል፡፡ በዞኑ በሰላም ግንባታ፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በጤናና በትምህርት ዘርፍ በተከናወኑ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ ወጤት እየተመዘገበ ስለመሆኑም ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከድህነት በመውጣት በምግብ ራስን ለመቻል በተተገበሩ የሌማት ትሩፋት መርሀግብርና ሌሎች ኢኒሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት መምጣቱንም ጠቁመዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በፓርቲው መሪነት በተለያዩ ዘርፎች በተከናወኑ የልማት ሥራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ነው ያስታወቁት። በዞኑ በልማትና በመልካም አስተዳደር በተሰሩ ሥራዎች እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የፓርቲው አመራሮችና አባላት የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል። በብልጽግና ፓርቲ የሀዲያ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ግዛው በበኩላቸው፤ የለውጡ መንግሥት የፖለቲካ ስልጣን ቅቡልነት በህዝብ ድምፅ ብቻ እንዲወሰን ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በሀገሪቱ የተጀመረውን የዴሞክራሲ ምህዳር በማጠናከር ለአዲሷ ኢትዮጵያ ግንባታ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የፓርቲው አባላት ተሳትፈዋል፡፡
ምርጫው ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው- ፓርቲዎች
Feb 27, 2026 53
ደሴ ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድና ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክሮች ለሀገርና ህዝብ በሚጠቅሙ የፖሊሲ አጀንዳዎች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል በአማራ ክልል ደሴ ከተማና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በደሴ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂደዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢና በኢዜማ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ ሻምበል ደምሌ ተረፈ፤ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርአት መዳበርና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ምርጫ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ የጋራ ምክር ቤቱ የዘንድሮው ምርጫ በሃሳብ የበላይነት በመፎካከር ሀገርን አሸናፊ የሚያደርግ እንዲሆን ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድና ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መሰረት እንዲሆን እየሰራን ነው ሲሉም ተናግረዋል። የዛሬው ውይይት ዋነኛ ዓላማም በምርጫው ሂደት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በጋራ በመፍታት ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ማካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢና በብልጽግና ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አለማየሁ፤ ለምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የጋራ ምክር ቤቱ አባላት በቅንጅት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። ለምርጫው ተወዳዳሪ እጩዎችንና ታዛቢዎችን መመልመላቸውን ጠቁመው በቅስቀሳ ወቅት ከጠብ አጫሪነትና ጥላቻ ንግግሮች በመራቅ መራጩ የጠራ ግንዛቤ አግኝቶ እንዲወስን ማድረግ የሁላችንም ሃላፊነት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባልና የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ተወካይ አቶ ያለው አሸብር፤ በሀገር ዘላቂ ሰላም፣ ጥቅምና ልማት ፓርቲያችን አይደራደርም ብለዋል። በወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ መሀመድ የሱፍ፤ በቅደመ ምርጫ፣ በምርጫና በድህረ ምርጫ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማስተካከል የዛሬው ምክክር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በሁሉም ፓርቲዎች ዘንድ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማስተካከል የተሳካ ምርጫ ለማካሄድ የተጀመረው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት ያስችላል
Feb 27, 2026 55
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት እንደሚያስችል የኢፌዲሪ የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በክልሎች፣ በከተማ አስተዳደሮችና በውጭ ዓለማት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የአጀንዳ ማሰባሰብና የተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ አካሂዷል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን በስኬታማነት ለማስቀጠል የሁሉም አካላት ሚናና ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድም የአጀንዳ ቀረፃና የግብዓት ማሰባሰብ የዝግጅት ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል። በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ በ1ኛ ዓመት አስቸኳይ ጉባኤም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የስራ ዘመን ለሁለተኛ ጊዜ ለሚቀጥሉት ስምንት ወራት ተራዝሟል። የኢፌዲሪ የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ኃይለየሱስ ታዬ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ብሔራዊ መግባባት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት፣ ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም በሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም ዙሪያ የዜጎችን ግንዛቤ በማሻሻል የዳበረ የዴሞክራሲ ሥርዓትን ለመገንባት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ተግባራትም የዜጎችን ግንዛቤ በማሳደግ ሕብረብሔራዊ አንድነትን እያጎለበቱ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በቀጣይም በክልሎች ጭምር የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል። የዜጎችን የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም ሥርዓት ግንዛቤ ለማጎልበትም በተለያዩ የህዝብና የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች መልዕክቶችና ትምህርቶች እየተላለፉ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክርም መግባባት ባልተደረሰባቸው ዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር የጋራ መግባባትን ለመፍጠር መሠረት የሚጥል መሆኑን ተናግረዋል። ለኢትዮጵያውያንም በሀገራዊ ምክክሩ የተመቻቸውን ዕድል በመጠቀም ብሔራዊ መግባባትን መፍጠርና ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት እንደሚያስችል አስገንዝበዋል። የሕገ-መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከልም ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት በዕውቀት ላይ የተመሰረቱ አጋዥ ሃሳቦችን በማፍለቅ እንደሚሰራ አንስተዋል።
በምርጫው የሀሳብ ልዕልና እንዲያሸንፍ ስልጡን የፖለቲካ ባህል እንከተላለን - ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች
Feb 27, 2026 59
ጎንደር፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ በጠቅላላ ምርጫው የሀሳብ ልዕልና እንዲያሸንፍ ስልጡን የፖለቲካ ባህል በመከተል የድርሻቸውን እንደሚወጡ በጎንደርና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀሳብ የበላይነት የሚያሸንፍበት እንዲሆን የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል እንደሚከተሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ/ኢዜማ/የጎንደር ቅርንጫፍ ተወካይ ዝናወርቅ ታደለ እንዳሉት፣ ፓርቲያቸው ትብብርና ፉክክርን መርህ ያደረገ የምርጫ ውድድር ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቅቋል። የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል በማራመድና በሃሳብ ልዕልና ላይ የተመሰረተ ምርጫ በማካሄድ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ግንባታ ለይ አሻራ እንደሚያኖሩ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም በጠቅላላ ምርጫው በንቃት ለመሳተፍ የምርጫ ምልክታቸውንና ማኒፌስቷቸውን ለሕዝብ እያስተዋወቁ መሆኑን ተናግረዋል። የቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት ተገኑ ደረጀ በበኩላቸው ፓርቲያቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ሥነ ምግባር ደንቡን አክብሮ ለውድድር እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ጥቅምንና የህዝብን ክብር ባከበረ መልኩ የሕዝብ ድምፅ ለማግኘት የምረጡኝ ቅስቀሳ እያካሄዱ መሆኑን ጠቁመዋል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ሀሳብ ላይ የተመሰረተ ክርክር ማካሄድ የስልጡን ፓርቲዎች ተግባር መሆኑንም ተፎካካሪ ፓርቲዎቹ ገልጸዋል።
የብልጽግና ፓርቲ የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ባደረጋቸው ጥረቶች የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ያስቀጥላል
Feb 27, 2026 76
ወልቂጤ ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፡- የብልፅግና ፓርቲ ያሉትን ፀጋዎች ወደ ውጤት በመቀየር የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ባደረጋቸው ጥረቶች የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ተገለፀ። የብልፅግና ፓርቲ በጉራጌ ዞን ''ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር'' በሚል መሪ ሃሳብ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመወዳደሪያ ምልክት (የስንዴ ነዶ) እና የማኒፌስቶ የማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በወልቂጤ ከተማ አካሄዷል። በወቅቱም የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንዳሉት፣ የብልፅግና ፓርቲ የህዝብ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ባደረጋቸው ጥረቶች ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል። በተለይም በየአካባቢው የሚገኙ ፀጋዎች ወደ ውጤት እንዲቀየሩ በተደረጉ ጥረቶች ውጤቶች መመዝገባቸውን አውስተው ለአብነትም በግብርናው ዘርፍ በእርሻና በእንስሳት ልማት የተገኘውን ውጤት አንስተዋል። ዞኑ ያለውን አቅም ለመጠቀም በተደረገው ጥረት በእርሻ ኢንዱስትሪ በመሰረተ ልማትና በሌሎችም የልማት ስራዎች የዜጎችን ህይወት ያሻሻሉ ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰው ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ፓርቲው አበክሮ ይሰራል ብለዋል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ስርዓትን በመዘርጋት በስንዴ ልማትና በምግብ ራስን ለመቻል በተሰሩ ስራዎች እንዲሁም ውብና ፅዱ አካባቢን በመፍጠር ረገድ የሃገራችን ስም በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍ ብሎ እየተወሳ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፓርቲው እነዚህን የልማት ስኬቶች ለማስቀጠል ይተጋል ያሉት አቶ ላጫ አሰባሳቢ ትርክትን በመገንባትና ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ ህዝቡን የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል እንደ ሀገር የተወጠነውን የልማትና የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ በትጋት ይሰራል ብለዋል። በጉራጌ ዞን ያለውን ፀጋ በመጠቀም አርሶ አደሩን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ በማድረግ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና የስራ እድል ለመፍጠር ያስቻሉ ውጤቶች መገኘታቸውን ያነሱት ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ገብረመስቀል ናቸው። ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተደረገው ርብርብ ፍሬ እያፈራ መሆኑን በመጠቆም የህዝቡ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አንስተዋል። ፓርቲው ሰው ተኮር ለሆኑ የልማት ስራዎች በሰጠው ልዩ ትኩረት የዜጎችን ህይወት የቀየሩ ውጤቶች መገኘታቸውን አንስተው በየጊዜው በዞኑ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚሰራም ተናግረዋል። በመድረኩም የዞንና የከተማ አስተዳደሮች የስራ ሃላፊዎች፣ የወጣትና ሴቶች አደረጃጀቶች እና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዘርባጃን ፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ጋር ተወያዩ
Feb 27, 2026 70
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዘርባጃን ፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በአዘርባጃን ባደረጉት የመጀመሪያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ላደረጉላቸው ሞቅ ያለ እና የተከበረ አቀባበል ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በአቪዬሽን ዘርፍ፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮች እና በነፃ የንግድ ቀጣናዎች፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እና በአዘርባጃን አቻው መካከል በተደረጉ የኢኮኖሚ ትብብሮች ላይ በመመስረት የሀገራቱ አጋርነት በየጊዜው እያደገ መምጣቱን አመልክተዋል። የትብብር ዘርፎቹ ለሁለትዮሽ ግንኙነት መጠናከር መሠረት የጣሉ ሲሆን፣ ዛሬ ከፕሬዝዳንቱ ጋር በተደረገው ጥልቅ ውይይትም ግንኙነቱን እና ትብብሩን ይበልጥ ለማጠናከር እና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ከስምምነት ላይ መደረሱን ተናግረዋል። የሀገራቱ መሪዎች በዛሬው ዕለትም በመከላከያ እና በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ የመግባቢያ ሰነዶች ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ መገኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክሮች ለሀገርና ህዝብ በሚጠቅሙ የፖሊሲ አጀንዳዎች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል- ምሁራን
Feb 27, 2026 132
ሮቤ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፡-የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክሮች ለሀገርና ህዝብ በሚጠቅሙ የፖሊሲ አጀንዳዎች ላይ ያተኮሩ መሆን እንዳለባቸው የመደ ወላቡ ዩኒቨርስቲ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ፖሊሲዎቻቸውንና ስትራቴጂዎቻቸውን በመገናኛ ብዙኃን ለሕዝብ ማስተዋወቅ ጀምረዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ እንዲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጎላ ሚና እንዳላቸው አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገልጸዋል። ፓርቲዎች በምረጡኝ ቅስቀሳቸው ከጥላቻ ንግግሮች መራቅና ሀሳባቸውን በሰለጠነ መንገድ መግለጽ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ያግዛል ነው ያሉት ምሁራኑ። ፓርቲዎቹ የሚያቀርቧቸው አማራጭ ሀሳቦች ወደ መሬት ሊወርዱ የሚችሉና ሀገርን የሚያሻግሩ ሊሆኑ እንደሚገባም አንስተዋል። በዩኒቨርስቲው የስነ ዜጋና ሥነ-ምግባር ትምህርት መምህርና ተመራማሪ መቅደስ መስፍን እንዳሉት፣ ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅሰቀሳ ወቅት በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሳተፉ ይገባል። ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ጊዜ ለሀገር የሚበጅና ሊያሻግር የሚችል አማራጭ ፖሊሲና ስትራቴጂያቸውን በሰለጠነ መልኩ ሊያንጸባርቁ ይገባል ብለዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒነት እንዲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የምርጫ ሥነ-ምግባር ሕጉን ባከበረ መልኩ መንቀሳቀስ አለባቸው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነትና ሥነ- ተግባቦት ትምህርት መምህርና ተመራማሪ ኡመር መሐመድኑር ናቸው። በአሁን ጊዜ ፓርቲዎቹ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን አማራጮች አያደረጉት ያለው ክርክር በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው በመከባበር ላይ የተመሰረተ ሲሆን ነው ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የጂኦግራፊና አካባቢ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ ተስፋዬ ፈዬ (ረዳት ፕሮፌሰር) በበኩላቸው የፓርቲዎች ንግግርም ሆነ ተግባር ህዝብን ያከበረ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ጊዜ የሚያነሱት አማራጭ ሀሳብ ሕብረተሰቡ በቀላሉ ሊረዳው በሚችለው አግባብ መቅረብ እንዳለበትም አንስተዋል። በምርጫው ቅስቀሳና ክርክር ወቅት የሀገርን አንድነትና ሉአላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ንግግርም ሆነ ተግባር መፈጸም ተገቢ እንዳልሆነ በመረዳት ፓርቲዎች ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ነው ረዳት ፕሮፌሰሩ ያስገነዘቡት። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው
Feb 27, 2026 72
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እና ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የኢዜማ፣ የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የአብን ፓርቲ አመራሮች ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የሁሉንም አካላት ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ ምክትል መሪ አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን እንዳሉት፥ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የምርጫው ሂደት ስኬታማነት ወሳኝ ነው። በሂደቱም መራጩ ሕዝብ፣ ገዥው ፓርቲ፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ተቋማት፣ ምርጫ ቦርድና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የየራሳቸው የጋራና የተናጠል ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። ትልቁ ዓላማችን የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መሆን አለበት ያሉት አርክቴክት ዮሐንስ እያንዳንዱ ባለድርሻ አካልና ዜጋ ሕግን በማክበር ሀገራዊ ሚናውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀ-መንበር አበራ በቀለ በበኩላቸው የዘንድሮው ምርጫ ለኢትዮጵያ የተረጋጋ ፖለቲካዊና ዲሞክራሲያዊ ጉዞ ጠንካራ መሠረት የምናኖርበት ነው ብለዋል። በምርጫው የሚያሸንፍ ሐሳብ ይዘን እንቀርባለን ያሉት አቶ አበራ ምርጫው ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ የዲሞክራሲ ምዕራፍ የሚያሻግር ወሳኝ የታሪክ አጋጣሚ መሆኑን አስገንዝበዋል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) የሥራ አስፈጻሚ አባል የሱፍ ኢብራሂም፥ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሽግግር በዲሞክራሲያዊ ምርጫና በሀሳብ የበላይነት ብቻ መሆን እንዳለበት ፓርቲያቸው በጽኑ እንደሚያምን ገልጸዋል። ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እጅግ ሰፊ ዝግጅትን የሚጠይቅ መሆኑን ጠቅሰው ይህም ከማኒፌስቶ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ቀበሌ ድረስ አማራጭ ሐሳብን የማስተዋወቅ ሥራ እንደሚጠይቅ አስረድተዋል። ምርጫ የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ አካል በመሆኑ፥ ፓርቲያቸው ለሀገር ወሳኝ በሆነው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቀዋል።
ማህበራዊ
የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ለሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን የኢፋ ቦሩ 2ኛ ጀረጃ ትምህርት ቤት ስጦታ አበረከተ
Feb 27, 2026 27
አምቦ ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦የቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጽህፈት ቤት በአምቦ ከተማ አስተዳደር ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን በተወለዱበት ኢላሞ ጎረምቲ ወረዳ ለሚገኘው ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን የኢፋ ቦሩ 2ኛ ጀረጃ ትምህርት ቤት ስጦታ አበረከተ። በሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን የጥበብ ስራዎች ውስጥ ትውልዱ ራሱን በማየት የሀገሩን አርት ለማሳደግ መትጋት አለበት ስጦታዎቹም የተለያዩ ኮምፒዩተሮች፣ ፕሪንተሮች፣ መፅሀፍቶች፣ የሚኒ ሚዲያ ቁሳቁሶች፣ የሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ፣ የህክምና መሳሪያዎች እና ሌሎች ለመማር ማስተማር የሚያገለግሉ ግብአቶች ነው። የቀዳማዊት እመቤት ፅህፈት ቤት ይህን ስጦታ ያበረከተው በአምቦ ከተማ የሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን 20ኛ አመት የዕረፍት መታሰቢያ ፕሮግራም ላይ ነው። ዛሬ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን የሚያስተምረው ትምህርት ቤቱ የተገነባው በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጽህፈት ቤት በ2015 ዓ.ም ሲሆን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመፅሀፍ ሽያጭ በተገኘ ገቢ ነው። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ)፤ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልእክት በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ስም ትምህርት ቤቱ መገንባቱ ትልቅ የታሪክ አሻራ መሆኑን አንስተው የአሁኑ ትውልድም ለጥበብ ስራዎች የሀገሩን ጥበብ ለማሳደግ መትጋት አለበት ብለዋል። የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ትምህርት ቤቱን ከማስገንባት ባለፈ፣ ለተማሪዎች የመማር ማስተማር ሂደት ግብዓት የሚሆኑ ልዩ ልዩ ድጋፎችን ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ለትምህርት ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ ላፕቶፖች፣ ፕሪንተሮችና ሌሎች የትምህርት መርጃ መሣሪያዎችን ጨምሮ በጠቅላላው 8 ሚሊዮን ብር የሚገመት ቁሳቁስ በስጦታ መልክ መበርከቱን ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ ከተገኙት አርቲስቶች መካከል አርቲስት አበበ ባልቻ፤ የሎሬቱ የጥበብ ሥራዎች በርካታ አርቲስቶችን በማፍራት በሀገራችን የጥበብ እድገት ውስጥ የማይረሳ አሻራ አኑረዋል ብሏል። የሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህንን አርአያነት በመውሰድ፣ የሀገራችንን ጥበብ አሁን ካለበት ለማሳደግ መስራት ይጠበቅብናል ብሏል። በመሆኑም በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጽህፈት ቤት በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ስም የተሰየመው የኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግሯል። አርቲስት ተፈሪ ዓለሙ፤ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ከኢትዮጵያ አልፎ የአፍሪካ የጥበብ እድገት በዓለም መድረክ እንዲታይ ያደረገ ታላቅ ባለውለታ መሆኑን ገልጿል። በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ስም ለተሰየመው የኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ በቀጣይ ሌሎች አርቲስቶችን በማስተባበር ድጋፍ እናደርጋለን በማለት አርቲስቶቹ ቃል ገብተዋል። የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ ደራራ ከተማ፤ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን የሀገራችንን አርት ለዓለም ያስተዋወቁ ድንቅ የሀገር ባለውለታ በመሆናቸው ታላቅ ክብር የሚገባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጽህፈት ቤት በሎሬቱ ስም ትምህርት ቤቱ በመገንባቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያን ክብርና ሉዓላዊነት በማስጠበቅ የአባቶቹን የዓድዋ ጀግንነት ታሪክ እያስቀጠለ ነው
Feb 27, 2026 24
ሰቆጣ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያን ክብርና ሉአላዊነት በማስጠበቅ የአባቶቹን የዓድዋ ጀግንነት ታሪክ እያስቀጠለ መሆኑን የሰራዊቱ አባላት ገለጹ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የመከላከያ ሠራዊት አመራሮችና አባላት የዓድዋን የጀግንነት ታሪክ በመድገም የሀገርን አንድነትና ዳር ድንበር የማስጠበቅ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም የተገኘ የአንድነት ውጤት ነው በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የሚገኙ የሠራዊቱ አባላት ለሀገር ሉዓላዊነትና ቀጣይነት ላለው ዕድገት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የዓድዋ ድል ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመውረር የነበረውን ሕልም ያከሸፈ ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ጮራን የፈነጠቀ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው። ከሰራዊቱ አመራሮች መካከል ሻለቃ ተክላይ አማረ፤ የዓድዋ ድል የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታና የሕዝቦች አንድነት በተግባር የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። ሠራዊቱ ዛሬም የአባቶቹን አርበኝነት በመውረስ የሕዳሴው ግድብን በመገንባት የዳግማዊ ዓድዋን ታሪክ በደማቁ ጽፏል ብለዋል። የዓድዋ ድል የውጭ ወራሪን ብቻ ሳይሆን የውስጥ ባንዳዎች ተልዕኮ የከሸፈበት መሆኑን ጠቅሰው፣ ሠራዊቱ በአሁን ጊዜ የሀገርን ሉዓላዊነት ለመፈታተን የሚሞክሩ የውስጥና የውጭ ኃይሎችን ድል የማድረግ ብቁ ቁመና ላይ ነው ብለዋል። የ204ኛ ኮር ሻምበል አዛዥ መቶ አለቃ እንድሪስ ጀማል፤ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ከቆሙ ለዓለም የሚተርፍ ታሪክ መስራት እንደሚችሉ ዓድዋ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። ሠራዊቱ ከጀግና አባቶች የተረከባትን ሀገር ዳር ድንበሯን አስጠብቆ ለተተኪው ትውልድ ለማስረከብና የተሰጠውን ግዳጅ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። ምክትል አስር አለቃ አጥቃቸው ሙሉዬ፤ ጀግኖች አርበኞች ዘመናዊ መሣሪያ የታጠቀውን ጠላት በሀገር ፍቅር ስሜት እንዳሸነፉት ሁሉ ዛሬም ሠራዊቱ ያንን ጽናት በመላበስ ማንኛውንም ተልዕኮ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ ነው ብለዋል። ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ልማት በትጋት የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት ነው ብለዋል። 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል ''ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ'' በሚል ሀሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል።
በሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን የጥበብ ስራዎች ውስጥ ትውልዱ ራሱን በማየት የሀገሩን አርት ለማሳደግ መትጋት አለበት
Feb 27, 2026 42
አምቦ ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ በሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን የጥበብ ስራዎች ውስጥ ትውልዱ ራሱን በማየት የሀገሩን አርት ለማሳደግ መትጋት አለበት ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ) ገለጹ። ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን 20ኛ ዓመት ህልፈተ ህይወት መርሃ ግብር መነሻውን በአዲስ አበባ ራስ መኮንን ድልድይ (70 ደረጃ) ከሚገኘው የሎሬቱ መታሰቢያ ሐውልት ጋር በማድረግ ወደ ሎሬቱ ትውልድ ከተማ አምቦ በማቅናት በተለያዩ ኹነቶች ተከብሯል። በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የኪነ-ጥበብና ስነ-ጥበብ ፈጠራ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ) በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ መርሃ ግብሩ የተዘጋጀው የሎሬቱን የጥበብ ትሩፋትና በጎ አሻራ ለወጣቱ ትውልድ ለማስተላለፍ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም የአሁኑ ትውልድ ራሱን በሎሬቱ የጥበብ ስራዎች ውስጥ በማየት የሀገሩን አርት ለማሳደግ ጠንክሮ መስራት አለበት ብለዋል። ለዚህም በየዓመቱ የሎሬት ፀጋዬን የአርት ስራዎች የሚዘክርና የሚያሳዩ ስራዎችን በቋሚነት ለመስራት ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ማቀዱንም ጠቁመዋል። የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ ደራራ ከተማ በበኩላቸው፤ ሎሬቱ የሀገራችንን አርት ለዓለም ያስተዋወቁ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ቢሮው መሰል የጥበብ ሰዎችን ለማፍራት የሚያስቸሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመው ይህንንም ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት አርቲስቶችም የሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህንን አርአያነት በመውሰድ፣ የሀገራችንን ጥበብ አሁን ካለበት ለማሳደግ ተባብረው እንደሚሰሩም ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ የተገኘው አርቲስት አበበ ባልቻ እንደገለፀው፤ የሎሬቱ የጥበብ ሥራዎች በርካታ አርቲስቶችን በማፍራት በሀገራችን የጥበብ እድገት ውስጥ የማይረሳ አሻራ አኑረዋል። አርቲስቱ አክሎም በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ስም ለተሰየመው የኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ሌሎች አርቲስቶችን በማስተባበር በየዓመቱ በመምጣት አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርጋለን ብሏል። ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን የኢትዮጵያን ጥበብ ከማሳደግ ባለፈ የአፍሪካ የጥበብ እድገት በዓለም መድረክ እንዲታይ ያደረገ መሆኑን የገለፀው ደግሞ አርቲስት ተፈሪ አለሙ ነው። ሀገራችን ኢትዮጵያን እንድንወድ ያደረገ ታላቅ አርቲስት ነው ሲልም ገልጿል።
በአማራ ክልል ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ምገባ ተጠቃሚ ሆነዋል
Feb 27, 2026 114
ባህር ዳር ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በትምህርት ቤት ምገባ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለፀ። ቢሮው የመማር ማስተማር ስራን የሚገመግም እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የሚመክር መድረክ በባህር ዳር ከተማ እያካሄደ ይገኛል። የቢሮ ኃላፊው አቶ ጥላሁን ወርቅነህ በመድረኩ እንዳስታወቁት፤ የመማር ማስተማር ስራውን በተሳትፎም ሆነ ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ቅንጅታዊ ስራዎች ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ነው። በአማራ ክልል የማህበራዊ ተቋማትን ደረጃ በማሻሻል ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ እየተደረገ ነው ከትምህርት ማህበረሰቡ ጋር በተደረገ የቅንጅት ስራ በጸጥታ ችግር ምክንያት ትምህርት አቋርጠው ከቆዩ ተማሪዎች በርካቶቹን ወደ ትምህርት ገበታ መመለስ እንደተቻለ ገልፀዋል። የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ ደረጃቸውን የጠበቁ ተቋማትን የመገንባትና አስፈላጊ ግብዓቶችን የማሟላት ተግባር በትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በዚህም ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የአራት ሞዴል ሁለተኛ ደረጃና የሦስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እየተፋጠነ ሲሆን በ2019 የትምህርት ዘመን ስራ ለማስጀመር ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል። በክልሉ መንግስትና በአጋር አካላት ትብብር በተመደበ አንድ ቢሊዮን ብር በጀት ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለም አስረድተዋል። የምገባ ፕሮግራሙም ተማሪዎች በትምህርታቸው ላይ እንዲያተኩሩ በማድረግ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ እና የማቋረጥ መጠንንም በመቀነስ ረገድ የጎላ ሚናን እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። ዘግይተው ወደ ትምህርት ቤት የመጡ ተማሪዎችን ለማብቃት በተፋጠነ የትምህርት አቀራረብና ማካካሻ የመማር ማስተማር ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል። በባህር ዳር ከተማና ዙሪያዋ በሚገኙ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ከ150 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ የገለጹት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ሙሉአለም አቤ (ዶ/ር) ናቸው። በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር በተያዘው የትምህርት ዘመን ከ286 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ የገለጹት ደግሞ የአስተዳደሩ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደስታው አለሙ ናቸው። ለሁለት ቀን በሚቆየው መድረክም የክልልና የዞን የዘርፉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ሲሆን ያለፉት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል።
ኢኮኖሚ
በደብረ ማርቆስ ከተማ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Feb 27, 2026 7
ደብረ ማርቆስ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በደብረ ማርቆስ ከተማ ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተመላከተ። በከተማዋ ወቅታዊ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ላይ ያተኮረ የወጣቶች ውይይት ተካሂዷል። በአማራ ክልል በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የወጣቶች ተጠቃሚነት እያደገ መጥቷል የከተማ አስተዳደሩ ስራና ክህሎት መምሪያ ምክትል ሃላፊ ዘሪሁን ደገፍ እንዳሉት፤ በከተማዋ ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው። በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ከ18 ሺ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ እስካሁን ባለው ሂደት ከ12 ሺ በላይ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል። ከተማ አስተዳደሩ ለወጣቶች የመስሪያና የመሸጫ ሼዶችን ከማመቻቸት ባለፈ ከ17 ሚሊየን ብር በላይ ብድር ማመቻቸቱንም ተናግረዋል። የከተማዋን ሁለንተናዊ ልማትና ዕድገት ለማረጋገጥ ወጣቶች የአካበቢያቸውን ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የከተማ አስተዳደሩ የሕዝብ ግንኙነትና አደረጃጀት ኃላፊ መልካሙ ሽባባው ፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት የነበረው የጸጥታ ችግር በኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ዘርፎች ላይ ጫና ማሳደሩን አስታውሰው አሁን ግን መሻሻሎች መኖራቸውን ገልጸዋል። ወጣቱ በከተማዋ የተገኘውን ሰላም ለማደናቀፍ የሚሞክሩ አካላትን በንቃት በመከላከል ተጠቃሚነቱን ሊያሳድግ ይገባል ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ጫኔ ታደለ፤ በንብ ማነብ ዘርፍ ተሰማርቶ ውጤታማ እየሆነ መሆኑን ጠቅሶ የአካባቢውን ሰላም ለመጠበቅ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል። ወጣት ምህረት መልካም በበኩሏ ሰርቶ መለወጥ የሚቻለው ሰላም ሲኖር በመሆኑ መንግስት ሰላምን ለማስፈን በሚያደርገው ጥረት ውስጥ የድርሻዋን እንደምትወጣ ተናግራለች።
በነቀምቴ ከተማ አስተዳደር በ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ወጪ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ ነው
Feb 27, 2026 51
ነቀምት፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል በነቀምት ከተማ በ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ መመለስ የሚያስችሉ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የነቀምቴ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ተመስገን ምሬሳ ለኢዜአ እንዳስታወቁት በበጀት ዓመቱ 16 አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል። በበጀት ዓመቱ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተከናወኑ ያሉ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች መመለስ የሚያስችሉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ከፕሮጀክቶቹ መካከል የኮሪደር ልማት፣ የአንድ መሶብ አገልግሎት መስጫ ማእከል ህንፃ፣ የውስጥ ለውስጥ የጎርፍ መፋሰሻ ቱቦዎች ቁፋሮና ጥገና ሥራ ይገኙበታል ብለዋል። እንዲሁም ለስራ እድል ፈጠራ የሚያገለግሉ ምርጥ ዘርያ ያላቸው ዶሮ መፈልፈያ ሼዶች፣ የአሳ ማራቢያ ገንዳዎች እና ሌሎችም የልማት ስራዎች መሆናቸውን አስረድተዋል። በተለይ የአንድ መሶብ አገልግሎት ህንፃ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በኮሪደር ልማት ስራም 8 ኪሎ ሜትር በላይ የአስፓልት መንገድ ዝርጋታ፣ የወለጋ ሙዚየም ግንባታ፣ የእግረኛ መንገድ፣ የሳይክል መጋለቢያ፣ የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎች እና የንግድ ቤቶች ስራ እንደሚያካትት አመላክተዋል። በልማት ፕሮጀክቶቹ ግንባታም በርካታ የከተማዋ ወጣቶች ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆናቸው ተናግረዋል። በነቀምቴ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ስራ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለነዋሪዎች ምቹ መዝናኛ ስፍራ እንደሚሆን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ጉተማ ተካልኝ በሰጡት አስተያየት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከተማዋ ከተጀመሩ የልማት እንቅስቃሴ ውሰጥ የኮሪደር ስራ ተጠቃሽ መሆኑን ገልጸዋል። ከተማን በማዘመን ለኑሮ ምቹ ለማድረግ መንግስት እንደ ሀገር የጀመረው የኮሪደር ስራ ነቀምቴንም ተጠቃሚ በማድረጉ መደሰታቸውን ተናግረዋል። አቶ መሸሻ ዘውዴ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ የልማት ስራዎች የከተማዋን እድገት የሚያፋጥኑና የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንደሚያቃልሉ ተናግረዋል። በተለይ ፕሮጀክቶቹ የከተማዋን ወጣቶች የስራ ባህል በመቀየር ገንቢ ሚና እንዳላቸው አስታውቀዋል። ወይዘሮ ሞቱ ደጀኔ በበኩላቸው የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ በፊት ቆሻሻ የሚጣልባቸው ቦታዎች ወደ አማረ መዝናኛ ስፍራዎች በመለወጥ የከተማዋ ገጽታን በመቀየር ውብ እያደረጋት መሆኑን አስረድተዋል። ደረጃቸውን የጠበቁ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እየተገነቡ መሆኑም ለነዋሪዎች ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር ባሻገር የትራፊክ አደጋን ለመከላከል እንደሚያስችል ጠቅሰዋል። በተለይ ለልማት ስራዎቹ ህብረተሰቡ ያሳየው ትብብር የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መብት መሰረት ባደረገ መልኩ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋ አፋጣኝ ምላሽ ማግኘት አለበት
Feb 27, 2026 70
ዲላ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ፈጣን የምጣኔ ሀብት እድገት የሚመጥንና ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መብቷን መሰረት ባደረገ መልኩ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋ አፋጣኝ ምላሽ ማግኘት እንዳለባት ምሁራን ገለጹ። ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ያለውን ምጣኔ ሃብቷን የሚሸከም የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋ ባጠረ ጊዜ ምላሽ ማግኘት እንዳለበት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። በዩኒቨርሲቲው የምጣኔ ሃብት መምህርና ተመራማሪ ታምራት በየነ(ዶ/ር) እንዳሉት የባህር በር የኢትዮጵያን ፈጣን የምጣኔ ሀብት እድገት የሚያጠናከር በመሆኑ ባጠረ ጊዜ ምላሽ ማግኘት ያለበት ጉዳይ ነው። በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ያለው የህዝብ ቁጥር ብቻ ሳይሆን የወጭ ንግዱም መሆኑን አንስተው ለዚህም በግብርና ዘርፍ በተለይ በቡና እንዲሁም በማዕድን ልማት የተገኘው ገቢ ተጨባጭ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት አዋጭና አመች ለሆኑ ሁኔታዎች ቅድሚያ ይሰጣል ያሉት ምሁሩ በዚህም የራሳቸው የባህር በር ያላቸው ሀገራት ተወዳዳሪነታቸውና ተጠቃሚነታቸው ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። በተለይ ኢትዮጵያ የምትገኝበት የቀይ ባህር ቀጣና ዓለምን በንግድ፣ በሰላምና በዲፕሎማሲ በማስተሳሰር ፈጣን እድገት ለማስመዝገብ ተመራጭ መሆኑን አስረድተዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያን ፈጣን የምጣኔ ሀብት እድገት የሚመጥንና ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መብቷን መሰረት ባደረገ መልኩ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋ አፋጣኝ ምላሽ ማግኘት እንዳለበት አስገንዝበዋል። የባህር በር ከምጣኔ ሀብት እድገት ባሻገር ራስን መጠበቅና ዓለም አቀፍ ትስስርን ማጠናከሪያ መንገድ በመሆኑ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የስነ-ትምህርት ዘርፍ ምሁሩ ፍሬዘር ዓለሙ(ዶ/ር) ናቸው። የባህር በር አጀንዳ በአጭር ጊዜ ውስጥ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ማግኘቱን አንስተው ይህም የኢትዮጵያ ጥያቄ ፍትሃዊና የጋራ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ መሆኑ ማረጋገጫ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር በመግፋት በቀጣናው የሚያተርፍ ሀገር የለም ያሉት ምሁሩ ለአፍሪካ ቀንድ የኢኮኖሚ እድገትና ለቀጣናው ሰላም ሲባል ኢትዮጵያ በአፋጣኝ የባህር በር ማግኘት እንዳለባት አስረድተዋል።
በአሪ ዞን በዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከ51ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል
Feb 27, 2026 56
ጂንካ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፡-በአሪ ዞን በዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከ51 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ዝግጅት መደረጉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለግብርና ሥራ ተስማሚ ስነ-ምህዳር፣ በቂ ውሃ እና ለም መሬት ካለባቸው አካባቢዎች አንዱ የአሪ ዞን ነው። የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ ለኢዜአ እንደገለጹት በአሪ ዞን ያለውን ሀብትና ፀጋ አሟጦ በማልማት የአርሶ አደሮችን ኑሮ ለመለወጥ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዞኑ በዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከ51 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስብጥር አመራረት ዘዴ ጥራጥሬዎችን እና ሆርቲካልቸር በማጣመር ለማልማት መታቀዱን ገልፀው፣ እስካሁንም ከ 41 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው መሬት ታርሶ ለዘር መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በበልግ አዝመራው ከ117ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ ገልጸው፣ በልማቱም የሆርቲካልቸር ምርቶችን ሳያካትት ከ4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘትመታቀዱንም አመልክተዋል፡፡ የበልግ አዝመራ ውጤታማነትን ለማሳደግም በሕብረት ሥራ ዩኒየኖች አማካኝነት የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እየቀረበ መሆኑንም አንስተዋል። ከዚህ ቀደም አርሶ አደሩ ውስንና የተለመዱ ሰብሎችን ብቻ ያለማ እንደነበር ያስታወሱት ኃላፊው፣ አሁን ላይ የስብጥር አመራረት ዘዴን በመከተል በአነስተኛ መሬት የተሻለ ጥቅም የሚያገኝበት አሰራር በመተግበር ውጤታማ እየሆነ መጥቷል ብለዋል። በዞኑ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን የመጠቀም ልምድ እያደገ ከመምጣቱ ባለፈ አርሶ አደሩ ሰብሎችን በኩታ ገጠም ማልማት በመጀመሩ የሰብል ምርታማነት በእጅጉ እያደገ መሆኑንም ነው የገለጹት። ቀደም ሲል ከሌሎች አካባቢዎች የሚመጡ ምርጥ ዘሮችን በአርሶ አደሮች ማሳ ማልማት መጀመሩን ገልፀው፣ በአሁኑ ወቅት የተሻሻሉ የስንዴ፣ የበቆሎና የማሽላ ዘር ብዜት በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በዞኑ ደቡብ አሪ ወረዳ አርሶ አደር የሆኑት አቶ ማሙሽ አዲሱ በዘንድሮ የበልግ አዝመራ የተሻለ ምርት ለማግኘት እየሰሩ እንዳሉ ገልጸዋል። በበልግ አዝመራ መሬታቸውን ለሦስት ጊዜ አርሰውና አለስልሰው ለዘር ሥራ ማዘጋጀታቸውን ገልፀው፣ በዘንድሮ የበልግ አዝመራ በቆሎ፣ ጎመን፣ ሽንኩርት፣ ቃሪያ፣ ካሮትና መሰል ሰብሎችን በስብጥር ለማልማት ማቀዳቸውን ገልጸዋል። በግብርና ባለሙያዎች ባገኙት ምክረ ሀሳብ መሰረት ጥራጥሬን ከአትክልትና ፍራፍሬ ጋር በማጣመር በስብጥር እያለሙ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ በዞኑ የባካ ዳውላ አሪ ወረዳ አርሶ አደር ግዛው አለሙ ናቸው። ጥራጥሬዎችን ከአትክልትና ፍራፍሬዎች ጋር አጣምሮ ማልማት ምርታማነትን በመጨመር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን እንደሚያሳድግ በተግባር አይተናል ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአዘርባጃን የሕዝብ አገልግሎት እና ማኅበራዊ ፈጠራ የመንግሥት ኤጀንሲን ጎበኙ
Feb 27, 2026 42
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው የአዘርባጃን የሕዝብ አገልግሎት እና ማኅበራዊ ፈጠራ የመንግሥት ኤጀንሲ (ASAN) የፈጠራ ማዕከልን ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ አዘርባጃን በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የሚመራ አስተዳደርን ለማስፋፋት እና የሕዝብ አገልግሎቶችን በዲጂታል ለማዘመን የምትከተለውን ስትራቴጂያዊ አካሄድ የሚያሳይ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሀገሪቱ የAI ኢንጂነሪንግ እና የአመራር ሥልጠና ዋና ማዕከል የሆነውን የAI አካዳሚን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ልዑኩ ጉብኝቱን በመቀጠል በክልሉ ውስጥ ካሉ ትላልቅ የነዳጅ እና የጋዝ ማቀነባበሪያ ማዕከላት አንዱ ወደሆነው ሳንጋቻል ተርሚናል እና ወደ አላት ነፃ የኢኮኖሚ ቀጣና አምርቷል። ጉብኝቶቹ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ፣ የኢነርጂ እና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትብብር ይበልጥ የማጠናከር አቅም እንዳላቸው ጽህፈት ቤቱ ገልጿል።
የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ለማሳለጥ ወጣቶችን በቴክኖሎጂ የማብቃት ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል
Feb 27, 2026 49
አምቦ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ለማሳለጥ ወጣቶችን በቴክኖሎጂ ለማብቃት ስራ ትኩረት መሰጠቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) አስታወቁ። የሰውሰራሽ አስተውሎት ትምህርትን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኦሮሚያ ክልል ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር በአምቦ ከተማ ያስገነባው የወጣቶች ኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ማዕከል እና የአምቦ ስታርት አፕ ማዕከል ተመርቋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ እና ሌሎች የፌዴራል እና የክልል አመራሮች ተገኝተዋል። በዚሁ ጊዜ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፣ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማስቀጠል ወጣቶችን በቴክኖሎጂ፣ በሳይንስና በፈጠራ ለማብቃት ስራ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል። ዛሬ በአምቦ ከተማ አገልግሎት የጀመረው ማዕከልም በአገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የኢኖቬሽን ሥነ-ምህዳር የማጠናከርና የቴክኖሎጂ ክፍተቶችን ለመሙላት ያግዛል ብለዋል። መሰል የኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ማዕከላት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተገንብተው የዜጎችን ችግር እየፈቱ መሆኑን ጠቅሰው የአምቦው ማዕከልም ወጣቶችን በቴክኖሎጂ በማብቃት የማኅበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የፈጠራ ሥራዎች የሚፈልቁበት ይሆናል ነው ያሉት። የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ በበኩላቸው፤ የአንድን ሀገር ዕድገት ማፋጠን የሚቻለው በቴክኖሎጂ ማገዝ ሲቻል መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ መንግሥት ግብርናንና ሌሎች ዘርፎችን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የሕዝቡን ኑሮ ለማሻሻልና የሀገሪቱን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግብ ለማሳካት ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። የአምቦ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃጫሉ ገመቹ፤ ማዕከሉ ወጣቶች የሚዝናኑበት ብቻ ሳይሆን፣ ዕውቀታቸውን ወደ ተግባር በመለወጥ ማኅበረሰባቸውን የሚያገለግሉበት የፈጠራ ማዕከል መሆኑን አብራርተዋል። በማዕከሉ የቴክኖሎጂ ሥልጠና የወሰዱ ወጣቶች በበኩላቸው፣ ባገኙት ዕውቀት ተጠቅመው የሀገሪቱን ዕድገት ለማፋጠን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በተለይም የድረ-ገጽ ማበልጸግ ሥልጠና በመውሰድ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ማኅበረሰብን በፈጠራ ለማገዝ መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።
በከተማዋ በተያዘው በጀት ዓመት ለአንድ መቶ ሺህ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ ለማዳረስ እየተሰራ ነው
Feb 27, 2026 52
ደገሃቡር፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በሶማሌ ክልል ደገሃቡር ከተማ በተያዘው በጀት ዓመት ለአንድ መቶ ሺህ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አብዲሀኪም መአሊን ገለጹ። የደገሃቡር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዲሀኪም መአሊን ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች ወጥ የሆነ ማንነት እንዲኖራቸው በማድረግ የተቀላጠፈና ዘመናዊ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው። ፋይዳ መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ ነው ፋይዳ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተቀመጠው ሀገራዊ ግብ እንዲሳካና ለዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመት በከተማዋ 100 ሺህ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እስካሁን ከ30 ሺህ በላይ ለሚሆኑት ተደራሽ መደረጉን አመልክተዋል። በከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል። ስልጠናው በቴክኖሎጂ የዳበረ ወጣት ለመፍጠር የላቀ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፣ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ዜጎች የዲጂታል መታወቂያውን በመያዝ ከሚሰጡ ዘመናዊ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል።
መቱ ዩኒቨርሲቲ በሚያካሄደው ማህበረሰብ ተኮር የጥናትና ምርምር ስራዎች የአካባቢውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ እያደረገ ነው
Feb 27, 2026 213
መቱ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ):- መቱ ዩኒቨርሲቲ በሚያካሄደው ማህበረሰብ ተኮር የጥናትና ምርምር ስራዎች የአካባቢውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ። በዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ዳይሬክቶሬት የግብርና ምርምር ዘርፍ አስተባባሪና መምህር ነዚፍ ሀምዛ ለኢዜአ እንዳሉት ዩኒቨርሰቲው ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በማካሄድ የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት እየሰራ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ በግብርና መስኮች ጥናትና ምርምር እያካሄደ ሲሆን ውጤቶችንም ወደ ተጨባጭ ስራ ለመቀየር ዘጠኝ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ለተግባራዊነቱ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከፕሮጀክቶቹ መካከል የሰብል እና የሆርቲካልቸር ምርጥ ዘር ዝግጅትና ብዜት፣ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ እንዲሁም ቨርሚ ኮምፖስት ቴክኖሎጂን ማስረጽ እንደሚገኙበት አስረድተዋል። በተለይ በሰብል ልማት እና በሆርቲካልቸር ከአከባቢው የአየር ንብረት ጋር ተስማሚ እና ምርታማነታቸው የተረጋገጠ ዝርያዎችን ለማባዛትና ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የፕሮጀክቶቹ ዋና ዓላማ የመማር ማስተማር ስራውን በተግባር የተደገፈ ከማድረግ ባለፈ የአካባቢው ማህበረሰብን ተጠቃሚ ማድረግ መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በውስጥ አቅም ራሳቸውን እንዲችሉ ያስቀመጠውን አቅጣጫ ለማሳካት ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ዩኒቨርሲቲው የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት እና የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትናን እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚያስችል አስረድተዋል። በዩኒቨሲቲው የዕጽዋት ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ መምህር ምስጋኑ ዋቅጅራ በበኩላቸው በምርምር የተገኘ ምርጥ የበቆሎ ዝርያን ለአርሶ አደሮች ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ለዚህም በ2017/2018 መኸር ከኢትዮጵያ የግብርና ግብአቶች ኮርፖሬሽን የነቀምቴ ቅርንጫፍ ጋር በመተባበር በ30 ሔሄታር መሬት ላይ የማባዛት ስራ መሰራቱን ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የምርት መሰብሰብ ስራው ተጠናቆ ለዘር የሚሆን 600 ኩንታል በቆሎ በማዘጋጀት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው የሆርቲካልቸር ዘርፍ መምህርና ተመራማሪ ሳሙኤል ታዬ ዩኒቨርሲቲው በግብርናው ዘርፍ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የችግኝ ጣቢያዎችን በማዘጋጀት ለመማር ማስተማር፣ ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ለማህበረሰብ አገልግሎትና ትስስር ስራዎቹ እየተጠቀመበት መሆኑን አንስተዋል። ይህም ዩኒቨርሲቲው የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ሀገራዊ ግቦች ለማሳካት የበኩሉን ድርሻ ለማበርከት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ወጣት ተመስገን ሂካ፣ መልካሜ ተሾመ እና አቶ ብርሃኑ ማሞ በፕሮጀክቱ ችግኝ ጣቢያዎች የስራ እድል የተፈጠረላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ሲሆኑ በስራው በሚያገኙት ገቢ ሕይወታቸውን እየመሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ያገኙትን ልምድ በመታገዝ የራሳቸውን ችግኝ ጣቢያ በማቋቋም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ማቀዳቸውን ተናግረዋል።
ስፖርት
ምድረ ገነት ሽሬ እና ሀዲያ ሆሳዕና ድል ቀንቷቸዋል
Feb 27, 2026 44
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ጨዋታዎች በመካሄድ ላይ ናቸው። በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መቻል እና ሃዋሳ ከተማ ነጥብ ተጋሩ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ምድረገነት ሽሬ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 1 አሸንፏል። ዳንኤል ዳርጌ እና ደሳለኝ ከተማው የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ደሳለኝ ከተማው በ96ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል ለቡድኑ ወሳኝ ሶስት አስገኝታለች። ናትናኤል ዳንኤል ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቸኛውን ግብ አስቆጥሯል። ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ምድረ ገነት ሽሬ በ26 ነጥብ ደረጃውን ከ15ኛ ወደ 10ኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ስድስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ24 ነጥብ ከነበረበት 11ኛ ደረጃ ወደ 13ኛ ዝቅ ብሏል። በሌላኛው መርሐ ግብር ሀዲያ ሆሳዕና ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 አሸንፏል።ደስታ ዋሚሾ በ79ኛው ደቂቃ ግቧን አስቆጥሯል። ወደ አሸናፊነት መንገድ የተመለሰው ሀዲያ ሆሳዕና በ27 ነጥብ ደረጃውን ከ13ኛ ወደ 9ኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ ሰባተኛ ድሉን አሳክቷል። በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ28 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ስድስት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መቻል እና ሃዋሳ ከተማ ነጥብ ተጋሩ
Feb 27, 2026 54
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር መቻል እና ሃዋሳ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሴናፍ ዋቁማ በ34ኛው ደቂቃ ባስቆጠረችው ግብ መቻል መሪ ሆኗል። ከእረፍት መልስ ብርቱካን ገብረክርስቶስ ጁላ በ74ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ላይ ያሳረፈችው ግብ ለሃዋሳ ከተማ አንድ ነጥብ አስገኝቷል። ለሃዋሳ ጎሉን ያስቆጠረችው ብርቱካን ገብረክርስቶስ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። ውጤቱን ተከትሎ መቻል በ31 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ሃዋሳ ከተማ በ29 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድል ቀንቶታል
Feb 27, 2026 47
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲዳማ ቡናን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል። በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ሪያል ማድሪድ ከማንችስተር ሲቲ ፒኤስጂ ከቼልሲ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ እሙሽ ዳንኤል ሁለት ግቦችን ስታስቆጥር ሰናይት ቦጋለ እና እፀገነት ግርማ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ እፀገነት ግርማ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። በሊጉ 12ኛ ድሉን ያስመዘገበው የወቅቱ የሊጉ የዋንጫ ባለቤት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ38 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ከሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሲዳማ ቡና በ18 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል።
በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ሪያል ማድሪድ ከማንችስተር ሲቲ ፒኤስጂ ከቼልሲ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Feb 27, 2026 83
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፦ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ዛሬ በስዊዘርላንድ ኒዮን ተካሄዷል። በዚሁ መሰረት ሪያል ማድሪድ ከማንችስተር ሲቲ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒኤስጂ ከቼልሲ ጋር የሚያደርገው ጨዋታም ትኩረትን ስቧል። በሊግ ምዕራፉ ሁሉንም ጨዋታዎች በማሸነፍ አንደኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል ከጀርመኑ ባየር ሌቨርኩሰን ጋር ይጫወታል። ጋላታሳራይ ከሊቨርፑል፣ ኒውካስትል ዩናይትድ ከባርሴሎና፣ አትሌቲኮ ማድሪድ ከቶተንሃም ሆትስፐርስ፣ አትላንታ ከባየር ሙኒክ እና ቦዶ ግሊምት ከስፓርቲንግ ሊዝበን ሌሎች በጥሎ ማለፉ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው። የጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ ጨዋታ መጋቢት 1 እና 2 ፣ የመልስ ጨዋታ መጋቢት 8 እና 9 ቀን 2018 ዓ.ም ይደረጋል። በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ በቀጥታ ያለፉ ስምንት ክለቦች የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ከሜዳቸው ውጪ ያደርጋሉ። በማጣሪያ ጥሎ ማለፉን የተቀላቀሉት ቀሪ ስምንት ክለቦች የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ከሜዳው ውጪ እንደሚያከናውኑ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር አስታውቋል። በተያያዘም የሩብ ፍጻሜ ድልድልም ይፋ ሆኗል። የሪያል ማድሪድ እና ማንችስተር ሲቲ አሸናፊ ከአትላንታ እና ባየር ሙኒክ አሸናፊ፣ የፒኤስጂ እና ቼልሲ አሸናፊ ከጋላታሰራይ እና ሊቨርፑል አሸናፊ፣ የባየር ሌቨርኩሰን እና አርሰናል አሸናፊ ከቦዶ ግሊምት እና ስፖርቲንግ ሊዝበን እንዲሁም የኒውካስትል ዩናይትድ እና ባርሴሎና አሸናፊ ከአትሌቲኮ ማድሪድ እና ቶተንሃም ሆትስፐርስ አሸናፊ በሩብ ፍጻሜው ይገናኛሉ። የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች በመጋቢት ወር መጨረሻ እና ሚያዚያ ወር መጀመሪያ ላይ ይካሄዳሉ። የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሀንጋሪ ቡዳፔስት ይካሄዳል።
አካባቢ ጥበቃ
የፕላስቲክ ከረጢት ክልከላን ለማሳካት ህብረተሰቡ እያደረገ ያለው ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል
Feb 27, 2026 50
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ህብረተሰቡ የፕላስቲክ ከረጢቶች ላይ የተጣለውን ክልከላ ተግባራዊ ለማድረግ እያበረከተ ያለውን አስተዋፅኦ አጠናክሮ እንዲቀጥል የኢፌዴሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። ባለስልጣኑ ከአምራቾች ጋር በመሆን ተኪ ምርቶች በስፋት ለተጠቃሚ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በሀዋሳ በፕላስቲክ ከረጢት ምትክ አማራጭ ምርቶችን የመጠቀም ልምድ እየዳበረ ነው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ 1383/2017 ከጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የፕላስቲክ ከረጢት ማምረት፣ ወደ ሃገር ማስገባት፣ መሸጥና መጠቀም ላይ ሙሉ ክልከላ ማድረጉ ይታወቃል። የኢፌዴሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ አዋጁ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የህዝብ ቁጥር፣ የከተሞች መስፋፋት እንዲሁም የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ስርዓት መዘርጋትን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ ነው። በለውጡ ዓመታት የተሰሩ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ፅዳት ማዕከል ያደረጉ እንዲሆኑ በማስቻል ንፁህና ፅዱ ለማድረግ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣመ አዋጅ ማዘጋጀት ማስፈለጉን ተናግረዋል። አዋጁ ለአንድ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ከረጢቶች(በተለምዶ ፌስታል የሚባሉት) ላይ ሙሉ በሙሉ ክልከላ ያደረገ አዋጅ መሆኑን አንስተዋል። አዋጁ የበርካታ ሀገራት ልምድን ከመቀመር ባለፈ የፕላስቲክ ከረጢቶች በጤና ላይ የሚያደርሱትን አሉታዊ ተፅዕኖ ታሳቢ በማድረግ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እነዚህ ፕላስቲክ ከረጢቶች ለካንሰር፣ ለአዕምሮ እድገት ውስንነት እና ለመተንፈሻ አካላት ህመሞች ምክንያት መሆናቸውን አንስተው፤ የአፈር ለምነትን፣ ውሃ አየር እና በእንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርስ እንደሆነ እንዲሁም የምግብ ዋስትናንና ሉዓላዊነትንም እንደሚያደናቅፍ አመልክተዋል። የፕላስቲክ ከረጢት አጠቃቀም ልምድን ለመቀየር ለአንድ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውሉ ፕላስቲክ ከረጢቶች ሙሉ በሙሉ መከልከላቸውን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅትም በአብዛኞቹ የሀገሪቷ አካባቢዎች ሕጉ ተፈፃሚ መሆኑን ጠቅሰው፤ ጥብቅ የክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የአዋጁ ትግበራ የጊዜ ገደብ ተራዝሟል የሚል ሃሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ህብረተሰቡ በዚህ የተሳሳተ መረጃ ሳይዘናጋ ለአዋጁ ተፈፃሚነት የበኩሉን ሚና መወጣቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። ባለስልጣኑ ከአምራቾች ጋር በመሆን አማራጭ ምርቶች በስፋትና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ እየሰራ መሆኑን አንስተው፤ በዚህም አብዛኛው ኢንዱስትሪዎች ምርቶችን በስፋት እያመረቱ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ አሁንም ምርትን በስፋትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ መስራት እንደሚጠይቅ ጨምረው አስታውቀዋል። በአካባቢ ላይ የሚደርሱ ብክለቶች ዙሪያ ጥቆማ የሚያደርሱበት እንዲሁም ቅሬታ የሚያቀርቡበት የዲጂታል ስርዓት ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር እየተዘረጋ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በክልሉ በተያዘው የበጋ ወራት ከ64 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የአፈርና የውሃ ጥበቃ የተፋሰስ ልማት እየተከናወነ ነው
Feb 27, 2026 53
ጋምቤላ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በተያዘው የበጋ ወራት ከ64 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የአፈርና የውሃ ጥበቃ የተፋሰስ ልማት በመከናወን ላይ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮ ኃላፊው አድሮው ቱት ለኢዜአ እንደገለጹት ምርታማነትን ለማሳድግ በበጋው ወራት የተጠናከረ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በክልሉ በሚገኙ ሶስቱም ዞኖች የአፈርና ውሃ ጥበቃ የተፋስ ልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የተፋሰስ ልማት ስራዎች በክልሉ በሚገኙ 13 ወረዳዎች በተመረጡ 101 ተፋሰሶች በመደበኛና በፕሮጀክቶች ከ64ሺህ ሄክታር በላይ በሚሸፍን መሬት ላይ እየተከወነ መሆኑን ተናግረዋል። በተፋሰስ ልማት ስራው ከአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች በተጓዳኝ ባለፈው ክረምትና ከዚያ በፊት በአረንጓዴ አሻራ ልማት ለተተከሉ ችግኞች እንክብካቤ እየተደረገ እንደሆነም አክለዋል። በክልሉ በበጋው ወራት እየተካሄደ ያለውን የአፈርና ውሃ ጥበቃ የተፋሰስ ልማት ስራዎች በመጪው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስነ-ህይወት ለማላበስ በ66 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች የማፍላት ስራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በመጪው ክረምት በሚከናወነው ለአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር ከሚዘጋጁት ችግኞች መካከል ከ8 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ከደንነት በተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።
የመሬት እንቅስቃሴ አደጋዎችን ለመቀነስ የመከታተያ ማዕከላት ማስፋፋት ያስፈልጋል - የዘርፉ ምሁራን
Feb 26, 2026 110
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ የመሬትመንቀጥቀጥና የእሳተ ገሞራ አደጋዎችን ለመቀነስ የመከታተያ ማዕከላት ማስፋትና የህዝብን ግንዛቤ ማሳደግ እንደሚያስፈልግ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ "የመሬት መንቀጥቀጥና የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ አደጋ በኢትዮጵያ ስጋትና መፍትሔዎች" በሚል መሪ ሃሳብ የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው። በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በተሰናዳው መድረክ የታደሙት የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ተከተል ዮሀንስ፤ ምሁራን በሀገራቸው ጉዳይ ያላቸውን ሚና ማላቅ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም በተለያዩ ሀገራዊ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ጥናትና ምርምር በማካሄድ ለሕትመትና ተደራሽነት እንዲበቁ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በኢትዮጵያ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚኖራቸውን መፍትሔ አመላካች የጥናትና ምርምር ሥራ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የጂኦ-ፊዚክስ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ ተመራማሪ ፕሮፌሰር አታላይ አየለ፤ የመሬት እንቅስቃሴ በተፈጥሮ ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል ብለዋል። በመሬትና በብዝኅ ህይወት ላይ የሚፈጥረው የገጽታ ለውጥም በህዝብ ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ አኗኗር ሥርዓት ከፍተኛ ጫና እንደሚያሳድር ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የሚከሰቱ የመሬት እንቅስቃሴዎችንም በመከታተል በተለያዩ ጊዜያት ህዝቡን የማስገንዘብ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት መንቀጥቀጥና የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ አደጋዎችን አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠትም የማዕከላትን መረጃ ማጠናቀር አቅም ማጎልበት እንደሚያስፈልግ አንስተዋል። የምህንድስና የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡት የጂኦቴክኒክ ኢንጅነሪንግ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አስራት ወርቁ በበኩላቸው፤ የመሬት እንቅስቃሴ አደጋዎችን ለመቀነስ የግንባታ ጥራትን ማስጠበቅ ይገባል ብለዋል። የህንፃና ተያያዥ መሰረተ ልማት ገንቢ ተቋማትና መሃንዲሶችም ከመሬት ሳይንስ ተመራማሪዎች ጋር በመቀናጀት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የመሬት መንቀጥቀጥ ማህበራዊ ገጽታን አስመልክቶ ጽሁፍ ያቀረቡት ፕሮፌሰር ተገኝ ገብረእግዚአብሔር፤ የስምጥ ሸለቆ የከተሜነት መስፋፋት ለመሬት እንቅስቃሴ አደጋ ተጋላጭነትን ከፍ ያደርጋል ብለዋል። ለዚህም የሀገራትን ተሞክሮ በመቀመር የቅድመ ማስጠንቀቂያና የመሠረተ ልማት ጥራትን ማጠናከር እንደሚገባ አስረድተዋል።
ለብሔራዊ ፓርኮችና ጥብቅ ሥፍራዎች ልማት የተሰጠው ትኩረት ከቱሪዝም ዘርፉ የበለጠ ለመጠቀም ያስችላል
Feb 26, 2026 206
ባህር ዳር ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡-ለብሔራዊ ፓርኮችና ጥብቅ ሥፍራዎች ልማት የተሰጠው ትኩረት ከቱሪዝም ዘርፉ የበለጠ ለመጠቀም የሚያስችል መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ በሀገሪቱ 29 ብሔራዊ ፓርኮችና 87 ዓይነት ጥብቅ ስፍራዎች ይገኛሉ ብለዋል። የጥብቅ ስፍራዎችን ማስፋፋት ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና የአካባቢ ጥበቃ ፋይዳው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ ጨበራ ጩርጩራ፣ አዋሽ እና ባሌ ብሔራዊ ፓርኮች ያሉ ሥፍራዎች ላይ የተሰሩ የልማት ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፉ ዕድገት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንም እንዲሁ። በጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ የሚታየውን ልዩ የዱር እንስሳት እንቅስቃሴ ለቱሪዝም መስህብነት ለማዋል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነም ነው ያብራሩት። በፓርኮች ውስጥ የሚስተዋሉትን ልቅ የእንስሳት ግጦሽ፣ የደን ጭፍጨፋ፣ ሕገ-ወጥ አደንና የእርሻ መስፋፋት ችግሮችን ለማስወገድ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ብለዋል። መንግስት የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስፋት ረገድ የሰጠው ልዩ ትኩረት ዘርፉ በፍጥነት እያደገ እንዲመጣ ማስቻሉንም ገለጸዋል። የአማራ ክልል አካባቢና ደን ጥበቃ ባለስልጣን ኃላፊ ተስፋሁን ዓለምነህ በበኩላቸው፤ በክልሉ የእንሰሳትና የብዝሃ ሕይወት የመጠበቅ ስራ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተሰራ ነው ብለዋል። በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚስተዋሉ ሰደድ እሳት፣ ህገወጥ እርሻ፣ ደን ጭፍጨፋ፣ ሕገ-ወጥ አደንና መሰል ተግባራትን ሕብረተሰቡን በማስተባበር የመጠበቅ ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። ፓርኩ ለአካባቢው ማሕብረሰብ ያለውን ጠቀሜታ ግምት ውስጥ በማስገባት ቀደም ሲል 136 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የነበረውን የፓርኩ ይዞታ ወደ 412 ስኩዌር ኪሎ ሜትር እንዲሰፋ መደረጉን አስታውሰዋል። ፓርኩን የማስፋት ስራ በዩኔስኮ መመዝገብ ስላለበት ይህንኑ ተግባር እውን ለማድረግ በጥናት ላይ መሰረት ያደረገ ሰነድ ተዘጋጅቶ መቅረቡን ተናግረዋል። የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አስማማው ዘገየ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው በተጓዳኝ በምርምርና በማሕበረሰብ አገልግሎት ፓርኩን እያገዘ ነው። የቱሪዝምና ቅርስ አስተዳደር የትምህርት ክፍል በመክፈት ተማሪዎች በተግባር የታገዘ ትምህርት እንዲወስዱ ከማድረግ ባሻገር ከተለያዩ የዓለም ሀገራት ጋር ግንኙነት በመፍጠር ሃብቱን የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ቀደም ሲል የተካሄደው የይዞታ ማስፋት ስራ የአካባቢውን ማሕበረሰብ የበለጠ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ የፓርኩ የሕግ ማስከበር ቡድን መሪ ሲሳይ ሰለሞን ናቸው። በማስፋት ስራውም ቀደም ሲል ያልተካተቱ ሥፍራዎች መካተታቸውን ጠቅሰው፤ ለዩኔስኮ የቀረበው ሰነድ ሲፀድቅ የፓርኩን ዓለም አቀፍ እውቅና ያሳድጋል ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የኢጋድ እና ተመድ ትብብር ለቀጣናዊ ሰላም
Feb 26, 2026 93
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት ያላቸውን የጋራ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የኢጋድ የደቡብ ሱዳን ልዩ ልዑክ አምባሳደር ሙሳ ጃማ አሊ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ጉዋንግ ኮንግ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። ልዩ ልዑኮቹ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት በተለይም በደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቅርቡ የአፍሪካ ህብረት የአምስት አባል ሀገራት ኮሚቴ (AU C5) እና ኢጋድ ያደረጉት የጋራ ጉባኤ የተገኙ ውጤቶች ላይም መክረዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ሰላም፣ መረጋጋት እና ቀጣናዊ ትብብር እውን እንዲሆን ያላቸውን ቅንጅት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ሩሲያ በትብብር መሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ
Feb 24, 2026 171
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ሩሲያ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ አጋርነት ዳይሬክተር ታትያና ዶቭጋሌንኮ ጋር በተቋሙ መቀመጫ ጅቡቲ ተወያይተዋል። በውይይቱ ወቅት ኢጋድ እና ሩሲያ በፖሊሲና ደኅንነት፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን፣ ሳይንስ እና ትምህርት ዘርፎች ትብብር ማጎልበት የሚያስችላቸውን ስምምነት እና የድርጊት መርሐ-ግብር ተፈራርመዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ ጉዳዮች ተቀራርበው ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ አጋርነታቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Feb 23, 2026 120
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ በሰላም፣ ልማት እና ዲፕሎማሲ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ(ኢ/ር) ከተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ አፍሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ ለረጅም ጊዜ የቆየ እና ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸው ትብብሩ በጥልቅ የባህል፣ የኢኮኖሚና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ላይ የተመሰረተ መሆኑን አውስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ በአፍሪካ ያላትን ዘላቂ ትብብር እና በአህጉሪቱ እያደገ የመጣውን ኢንቨስትመንት አልፎም በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ያላትን ገንቢ ሚና አድንቀዋል። ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመቀናጀት በሊቢያ፣ ሱዳን እና ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች እያሳየች ያለውን የዲፕሎማሲ ድጋፍ እና ተሳትፎ አዎንታዊ መሆኑን አመልክተዋል። የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ በበኩላቸው የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ በልማት፣ በሰላም እና በባለብዙ ወገን ትብብር ያለውን የመሪነት ሚና አንስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ልማት፣ ሰላም፣ ደህንነት እና ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላትን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች የአፍሪካ ህብረትና ሳዑዲ አረቢያ ያላቸውን ግንኙነት በጋራ መከባበር መንፈስ፣ በወዳጅነት እና በስትራቴጂካዊ አጋርነት ላይ በመመስረት የበለጠ ለማጠናከር የጋራ ፍላጎት ማሳየታቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና የፈጠረውን የንግድ ትስስር ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት ወሳኝ ነው
Feb 21, 2026 180
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን የንግድ ትስስር ዕድል በአግባቡ ለመጠቀም በመንግሥታትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለ አጋርነትን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የስምምነቱ ትግበራ የንግድ መሰናክሎችን በማስቀረት የሀገራትን የንግድ ልውውጥ ለማሳለጥ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተ ነው። እስካሁን 50 ሀገራት ፈርመው ያጸደቁት ይህ የንግድ ቀጣና፤ በዲጂታል የኢኮኖሚ ዕድገት የፋይናንስ ቴክኖሎጂን በማስፋት የአኅጉሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በማዘመንና የገንዘብ ዝውውርን በማቀላጠፍ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት የአሰራር ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተዳራሽ ለማድረግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ዘርግቷል የኢትዮጵያ ቱሪዝም አዲሱ ገጽታ፤ ከአማራጭ ማጣት ወደ መዳረሻዎች ብዛት በኢትዮጵያ ለግል ዘርፉ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ ኢኮኖሚው እየተነቃቃ ነው የአፍሪካን የተፈጥሮ ሃብትም በተሻለ የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነት በማልማት የመሰረተ ልማት፣ የዋጋ ግሽበትና የንግድ መሰናክሎችን ለመቀነስ አይነተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም አስረድተዋል። በዚህም አባል ሀገራት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን በማፋጠን የእርስበርስ የንግድ ልውውጥን ማሳለጥ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን ዕድል ለመጠቀም የግሉ ዘርፍና የአባል ሀገራት መንግሥታት የእርስ በርስ የንግድ ልውውጥን ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሰረትም የአባል ሀገራት ኢንቨስትመንትን የሚያነቃቃ የኢንቨስትመንት ጥበቃ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስረድተዋል። የስምምነቱ የኢንቨስትመንት ጥበቃም የአፍሪካን በመተማመን ላይ የተመሰረተ የእርስበርስ ንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ለማጎልበት የሚያስችል መሆኑን አስታውቀዋል።
ሐተታዎች
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 164
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 191
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 636
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 972
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 183
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 293
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1045
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1011
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3524
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2344
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8139
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6622
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 99
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 215
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።