ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ከ17ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ልማት ይሸፈናል
Dec 23, 2025 2
ዲላ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት ያረጀ ቡና በማንሳትና ማሳውን በማስፋት ከ17ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ልማት ለመሸፈን እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ቡናና ቅመማቅመም ባለስልጣን ገለጸ። ቡናን በኩታ ገጠም በማልማት የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ አቅም የማሳደጉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አማኑኤል ብሩ ተናግረዋል። ቡናን በኩታ ገጠም የማልማት ኢኒሼቲቭ በክልሉ ጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ ዛሬ በባለድርሻ አካላት የመስክ ምልክታ ተካሂዷል። የክልሉ ቡናና ቅመማቅመም በወቅቱ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በክልሉ የቡና ማሳን በማስፋትና በማደስ የዘርፉን ልማት ለማሳደግ እየተሰራ ነው። ለአብነትም ባለፈው ዓመት ከ7ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና በማልማት የክልሉን የቡና ሽፋን ወደ 235 ሺህ ሄክታር ማሳደጉንና ከዚህም ውስጥ በኩታ ገጠም የለማ እንደሚገኝበት ገልጸዋል። በክልሉ የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉ የቡና ዝሪያዎች የማቅረብና በኩታ ገጠም ማልማት ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ተግባሩን በማስቀጠልም በተያዘው በጀት ዓመት ያረጀ ቡና በማንሳትና ማሳውን በማስፋት ከ17ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ልማት ለመሸፈን በሂደት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥም ከ3ሺህ 707 ሄክታር በኩታ ገጠም ይለማል ያሉት አቶ አማኑኤል፤ ለዚህም የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት፣ የተሻሻሉ የቡና ዝሪያዎች አቅርቦትና አስፈላጊ ግብዓቶች ማቅረባቸውን አንስተዋል። በዞኑ ዝርያቸው የተሻሻሉ ቡናን ማልማት ምርታማነትን ከማሳደጉ ባለፈ ምርቱ የሚደርስበትን ጊዜውን ማሳጠር መቻሉን የገለጹት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ ተገኝ ታደሰ ናቸው። በዞኑ የኩታ ገጠም የቡና ልማት አርሶ አደሩንና ቀበሌዎችን በልማት እያስተሳሰረ ነው ያሉት ሃላፊው፤ ለአብነትም በወናጎ ወረዳ የቱማታ ጭራቻና ጦቅቻ ቀበሌዎች መካከል የሚገኘው አንድ መቶ ሄክታር ኩታ ገጠም ጥሩ ማሳያ ነው ብለዋል። በወናጎ ወረዳ ቱማታ ጭራቻ ቀበሌ አርሶ አደር አስራት ጨበሶ በሰጡት አስተያየት፤ በቀበሌያቸው እሳቸውን ጨምሮ አንድ መቶ አርሶ አደሮች ቡናን በኩታ ገጠም እያለሙ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ የተሻሻለው የቡና ዝሪያ ድርቅና በሽታ ከመቋቋም ባለፈ በሁለት ዓመት ውስጥ የመጀመሪያ ምርት ለመስጠት አበባ መያዙ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።  
የቱሪስት መስህብ መዳረሻ ሥፍራዎችን የማልማቱ ተግባር ይጠናከራል - ሚኒስቴሩ
Dec 23, 2025 21
ቦንጋ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ተፈጥሯዊና ታሪካዊ የቱሪስት መስህብ መዳረሻ ሥፍራዎችን የማልማቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የቱሪዝም ሚኒስቴር ገለጸ። በሚኒስቴሩ እና ቱር ኢትዮጵያ የተመራ ቡድን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ካፋ ዞን የቱሪስት መዳረሻዎችን ጎብኝቷል። በቱሪዝም ሚኒስቴር የመረጃ ሲነየር ባለሙያ አለማየሁ ወርቅነህ በወቅቱ እንዳሉት፤ እንደሀገር የቱሪዝም ዘርፉን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ አቅም ለማሳደግ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስተዋወቅ በትኩረት እየተሰራ ነው።   በተለይም ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህብ ሥፍራዎችን የማልማቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጠል ገልጸዋል። በዚህ ረገድ በካፋ ዞን በርካታ ተፈጥሯዊና ታሪካዊ የቱሪስት መስህቦች እንደሚገኙ በጉብኝታቸው መመልከታቸውን አንስተዋል። ህብረተሰቡም የተፈጥሮ ምህዳርን ያስጠበቀ ደንን ለቱሪስት መስህብነት ማዋሉ የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተገነቡ የገበታ ለሀገርና ለትውልድ የቱሪስት መዳረሻዎች ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ ማነቃቃታቸውን የገለጹት ደግሞ በክልሉ ባሕል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የማርኬቲንግና ፕሮሞሽን ዳይሬክተር ለምለም አስራት ናቸው። የክልሉን የቱሪስት ሀብቶችን በማስተዋወቅና የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ለማብቃት በቅንጅት መሰራቱን አንስተዋል።   በክልሉ የቱሪስት መዳረሻዎችን፣ በጥናት የመለየት፣ ፓኬጅ የመቅረፅና ማፕ የማዘጋጀት ስራም እንዲሁ። በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የካፋ ዞን ባሕል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ ታሪኳ ታከለ በበኩላቸው፣ በዞኑ 138 ተፈጥሯዊ፣ ታሪካዊና ባህላዊ የቱሪስት መዳረሻዎች መለየታቸውን ተናግረዋል። እነዚህን የቱሪስት መዳረሻዎች በተገቢው ለይቶ ለማልማትና ለማስተዋወቅ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በጉብኝቱ ከተሳተፉ የቱሪዝም ጋዜጠኞች መካከል ዘሪሁን ግርማ፤ ጉብኝቱ የቱሪዝም ሀብቶች ይበልጥ በማስተዋወቅ የዘርፉን ሁለንተናዊ አቅም ለማጎልበት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግሯል። በዚህ ረገድ በካፋ ዞን የቱሪስቶችን ቀልብ የሚስቡ በርካታ መዳረሻዎች እንዳሉ መረዳቱን አንስቷል።  
የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላችንን እንወጣለን-የመተማ ወረዳ ነዋሪዎች
Dec 23, 2025 38
መተማ፤ ታህሳስ14/2018 (ኢዜአ):-የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ አስተዳደር ነዋሪዎች ተናገሩ። በመተማ ወረዳ ጉባይ ጀጀቢት ከተማ ዘላቂ ሰላም ግንባታን መሰረት ያደረገ ሕዝባዊ ውይይት ዛሬ ተካሄዷል።   በውይይት መድረኩ ላይም ነዋሪዎቹ ፤ የአካቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ሙሉነህ ጥጋቡ ፤ በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም በማፅናት ልማት እንዲጠናከር የሚደግፉ መሆኑን ገልጸዋል። ሕግ የማስከበር ተግባር ተጠናክሮ የሰፈነውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል። ሌላኛው ተሳታፊ አቶ ክፍሌ ለጋስ ፤ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ለሁሉም ነገር ሰላም አስፈላጊ ነው ያሉት ቄስ አሰፋ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ መንግስት ለዘላቂ ሰላም እያደረገ ያለውን ተግባር እንደሚደግፉ አስታውቀዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፤ሕዝቡ በሰላም ማስከበር ተግባር የነቃ ተሳትፎውን ይበልጥ ማጠናከር ይኖርበታል። መንግስት ሰላምን ለማፅናት እያደረገ ያለው የሕግ ማስከበር ተግባር ውጤት እያመጣ መሆኑን አንስተዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረሰ አዱኛ፤ መንግስት ከሕግ ማስከበር ስራ ጎን ለጎን የሰላም አማራጭን ለሚቀበሉ በሆደ ሰፊነት አሁንም በሩን ከፍቷል ብለዋል። ሆኖም በሽፍትነት በመቀጠል ሕዝቡን ሰላም በሚነሱት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አረጋግጠዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዘላቂ ጥቅም ያስገኛል
Dec 23, 2025 47
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የንግድ ልውውጥ እና የአገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዘላቂ ጥቅም እንደሚያስገኝ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም አሊ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም አሊ የዲጂታል 2030 ስትራቴጂን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የዘመናችን በራሷ የምትተማመን ኢትዮጵያ፣ ብልጽግና በሁሉም ክልሎቿ ለማረጋገጥ የሚያስችል ቁልፍ ስትራቴጂ መሆኑን አመልክተዋል። ስትራቴጂው ለእያንዳንዱ ዜጋ የሚያገለግል፣ አገልግሎት አሰጣጥን የሚያዘምን፣ ኢኮኖሚን የሚያሳድግና እያንዳንዱ ዜጋ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት እንዴት ተሳትፎ ማድረግ እንደሚችል እንደሚያሳይ ተናግረዋል።   ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ያስፈለገው የሰው ሰራሽ አስተውሎት በፍጥነት ማደግ፣ የዜጎች ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት የማግኘት መሻት እና የንግድ ዘርፉ የበለጠ በዲጂታል ዘርፍ መደገፍ ወሳኝ በመሆኑ ምክንያት እንደሆነ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በጀመረችው የዲጂታል ጉዞ በቁርጠኝነት ካልቀጠለች የዲጂታል ክፍፍል እየሰፋ ይመጣል ያሉት አማካሪዋ ስትራቴጂው ያንን ክፍፍል የሚያጠብ እንደሆነ ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አካታች ሉዓላዊ እና በግልጽ አላማ የሚመራ መሆኑንም ነው ጨምረው ያብራሩት። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ መሰረት ጣይ እንደሆነ ገልጸው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የበለጠ ዘርፉን በጥልቀት እንደሚያሰፋ ገልጸዋል። ይህም ከሙከራ ፕሮጀክቶች ወደ ሀገር አቀፍ ስርዓቶችና ከተከፋፈሉ አሰራሮች ወደ ተቀናጁ አገልግሎቶች ለመሸጋገር ያስችላል ነው ያሉት። ሰዎች እና ተቋማትን ማብቃት፣ ሁሉን አቀፍ ዲጂታል ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣ አካታች የኢኮኖሚ እድገት ማፋጠንና ኢትዮጵያ ዋnኛ የዲጂታል መዳረሻ ማድረግ የስትራቴጂው የስኬት መለኪያዎች መሆናቸውን አመልክተዋል።   የኤሌክትሪክ ኃይል፣ ትስስር እና ተአማኒነት የስትራቴጂው ምሰሶዎች መሆናቸውንም ነው ጨምረው አማካሪዋ የገለጹት። በስትራቴጂው አማካኝነት የህዝብ ዲጂታል መሰረተ ልማት የመንግስት አገልግሎቶችን በማዘመንና የዲጂታል አሰራሮችን በማስፋት ዘላቂ የኢኮኖሚ ጠቀሜታን የማስገኘት ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። ከቴክኖሎጂ በተጨማሪ ስትራቴጂው ህጎች፣ መረጃዎች፣ ክህሎት እና ታማኝነት ወሳኝ መሆናቸው በግልጽ መቀመጡን አስረድተዋል። ስትራቴጂው ግብርና፣ ጤና፣ ትምህርት እና ኢንዱስትሪን እንዲሁም ሌሎች ዘርፎችን ያካተተ፣ ሀገር በቀል እና ሰውን ያማከለ እንደሆነም ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሃይል እና የኢንተርኔት ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣ የተሻሻለ የህዝብ አገልግሎት መዘርጋት፣ ዳታ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን መስጠት፣ የግል ዘርፍ አቅምን ጠንካራ ማድረግ፣ ለሳይበር ጥቃት በቂ የመከላከል ዝግጁነት መገንባትና ኢትዮጵያን የዲጂታል መሪነት ማጎናጸፍ የስትራቴጂው መዳረሻ ግቦች መሆናቸውን አመልክተዋል። የዲጂታል አማካሪዋ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እንዲሳካ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የሚታይ
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዘላቂ ጥቅም ያስገኛል
Dec 23, 2025 47
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የንግድ ልውውጥ እና የአገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዘላቂ ጥቅም እንደሚያስገኝ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም አሊ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም አሊ የዲጂታል 2030 ስትራቴጂን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የዘመናችን በራሷ የምትተማመን ኢትዮጵያ፣ ብልጽግና በሁሉም ክልሎቿ ለማረጋገጥ የሚያስችል ቁልፍ ስትራቴጂ መሆኑን አመልክተዋል። ስትራቴጂው ለእያንዳንዱ ዜጋ የሚያገለግል፣ አገልግሎት አሰጣጥን የሚያዘምን፣ ኢኮኖሚን የሚያሳድግና እያንዳንዱ ዜጋ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት እንዴት ተሳትፎ ማድረግ እንደሚችል እንደሚያሳይ ተናግረዋል።   ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ያስፈለገው የሰው ሰራሽ አስተውሎት በፍጥነት ማደግ፣ የዜጎች ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት የማግኘት መሻት እና የንግድ ዘርፉ የበለጠ በዲጂታል ዘርፍ መደገፍ ወሳኝ በመሆኑ ምክንያት እንደሆነ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በጀመረችው የዲጂታል ጉዞ በቁርጠኝነት ካልቀጠለች የዲጂታል ክፍፍል እየሰፋ ይመጣል ያሉት አማካሪዋ ስትራቴጂው ያንን ክፍፍል የሚያጠብ እንደሆነ ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አካታች ሉዓላዊ እና በግልጽ አላማ የሚመራ መሆኑንም ነው ጨምረው ያብራሩት። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ መሰረት ጣይ እንደሆነ ገልጸው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የበለጠ ዘርፉን በጥልቀት እንደሚያሰፋ ገልጸዋል። ይህም ከሙከራ ፕሮጀክቶች ወደ ሀገር አቀፍ ስርዓቶችና ከተከፋፈሉ አሰራሮች ወደ ተቀናጁ አገልግሎቶች ለመሸጋገር ያስችላል ነው ያሉት። ሰዎች እና ተቋማትን ማብቃት፣ ሁሉን አቀፍ ዲጂታል ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣ አካታች የኢኮኖሚ እድገት ማፋጠንና ኢትዮጵያ ዋnኛ የዲጂታል መዳረሻ ማድረግ የስትራቴጂው የስኬት መለኪያዎች መሆናቸውን አመልክተዋል።   የኤሌክትሪክ ኃይል፣ ትስስር እና ተአማኒነት የስትራቴጂው ምሰሶዎች መሆናቸውንም ነው ጨምረው አማካሪዋ የገለጹት። በስትራቴጂው አማካኝነት የህዝብ ዲጂታል መሰረተ ልማት የመንግስት አገልግሎቶችን በማዘመንና የዲጂታል አሰራሮችን በማስፋት ዘላቂ የኢኮኖሚ ጠቀሜታን የማስገኘት ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። ከቴክኖሎጂ በተጨማሪ ስትራቴጂው ህጎች፣ መረጃዎች፣ ክህሎት እና ታማኝነት ወሳኝ መሆናቸው በግልጽ መቀመጡን አስረድተዋል። ስትራቴጂው ግብርና፣ ጤና፣ ትምህርት እና ኢንዱስትሪን እንዲሁም ሌሎች ዘርፎችን ያካተተ፣ ሀገር በቀል እና ሰውን ያማከለ እንደሆነም ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሃይል እና የኢንተርኔት ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣ የተሻሻለ የህዝብ አገልግሎት መዘርጋት፣ ዳታ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን መስጠት፣ የግል ዘርፍ አቅምን ጠንካራ ማድረግ፣ ለሳይበር ጥቃት በቂ የመከላከል ዝግጁነት መገንባትና ኢትዮጵያን የዲጂታል መሪነት ማጎናጸፍ የስትራቴጂው መዳረሻ ግቦች መሆናቸውን አመልክተዋል። የዲጂታል አማካሪዋ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እንዲሳካ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ትኩረት ተሰጥቶታል
Dec 23, 2025 43
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ሙሉ ለሙሉ ተደራሽ የማድረግ ስራ ይከናወናል ሲሉ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ገለጹ። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። በመርሃ ግብሩ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች ባቀረቡት ማብራሪያ፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ማሳደግ፣ የመንግስት ገቢን መጨመርና የተቀናጀ የመረጃ ስርዓት መዘርጋት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።   የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያሥላሴ፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ ቁልፍ ጉዳይ ሆኖ መተግበሩን አስታውቀዋል። የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ማዳረስ በመንግስት የመቶ በመቶ እቅዶች ውስጥ መካተቱን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት 30 ሚሊየን የሚደርሱ ዜጎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ፋይዳ ትኩረት የተሰጠው በመሆኑ ሙሉ ለሙሉ ተደራሽ የማድረግ ስራ ይከናወናል ብለዋል። በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ሀገራዊ ንቅናቄ በማድረግ 90 ሚሊየን ዜጎችን የፋይዳ መታወቂያ ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን አስታውቀዋል፡፡   የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታዬ ግርማ በበኩላቸው፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂዎች በዜግነት አገልግሎት ላይ ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን ተናግረዋል። ለአብነትም በአዲስ አበባ ከማዕከል እስከ ወረዳ የተዘረጋው የዲጂታል ትስስር ለዚህ ተጠቃሽ ስኬት መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። በሀገር ውስጥ አቅም የለሙ መተግበሪያዎች ለቤተሰብ ምዝገባ፣ ለወሳኝ ኩነትና ለነዋሪዎች አገልግሎት መዋል መጀመራቸውን ገልጸው፤ ይህም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተቋማትን በመረጃ ለማስተሳሰር መሰረት ተጥሏል ነው ያሉት።
በሳይበር ደህንነት ወር የህብረተሰቡን ንቃተ-ህሊና ማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎች ተከናውነዋል
Dec 23, 2025 37
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ በስድስተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር የዜጎችንና የተቋማትን የሳይበር ደህንነት ግንዛቤ ማጎልበት የሚያስችል ስራ መከናወኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ገለጹ። "የሳይበር ደህንነት የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት" በሚል መሪ ሀሳብ ከጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው ስድስተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር የማጠቃለያ እና የእውቅና መርኃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ጨምሮ ለሳይበር ደህንንት ወሩ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት እውቅና ተሰጥቷቸዋል።   የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የዘንድሮው የሳይበር ደህንነት ወር በስሉጥ ከተማ ግንባታ እና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭት መከላከል ላይ ያተኮረ እንደነበር ጠቁመዋል። በዚህም አቅምን ከመገንባት አኳያ ትልቅ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው የህበረተሰቡንና የተቋማትን የሳይበር ደህንነት ግንዛቤ ማጎልበት የሚያስችል ስራ መከናወኑን አመላክተዋል። ኢትዮጵያ ብሩህ አዕምሮ ያላቸው ዜጎች ያሏት ሀገር መሆኗን ገልጸው አስተዳደሩ ለባለተሰጥኦ ወጣቶችና ታዳጊዎች ስልጠና በመስጠት እያበቃ እንደሚገኝ ተናግረዋል።   ወሩ ሀገር በቀል እውቀቶችን በስፋት ማስተዋወቅ የተቻለበት መሆኑን አንስተው ወጣቶች ያሏቸውን የሳይበር ደህንነት ክህሎቶች በተለያዩ ውድድሮች ማቅረባቸውን ጠቅሰዋል። በወሩ በአጭር ፊልም ውድድር አንደኛ እና ሁለተኛ የወጡት ዘር አዳም አሰፋ እና አቤነዘር አዲስ በሀሰተኛ መረጃ ስርጭት እና በስልክ የሚፈጸሙ የማጭበርበር ድርጊቶች ዙሪያ የሠሯቸው ፊልሞች ለሽልማት እንዳበቋቸው ተናግረዋል። የተሰጣቸው እውቅና ለላቀ ስኬት የሚያነሳሳ መሆኑን በመጥቀስ፥ በቀጣይ በመሰል ሀገራዊ ሥራዎች ላይ ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
በባንኩ ለአርሶ አደሩ የተመቻቸው የብድር አማራጭ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዝ ነው - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)
Dec 23, 2025 56
ሆሳዕና፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአርሶ አደሩ ያመቻቸው የብድር አማራጭ በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚያግዝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ባንኩ በግብርናው ዘርፍ አርሶ እና አርብቶ አደሩን ለመደገፍ ባመቻቸው የብድር አማራጭ ላይ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ከባንኩ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ዛሬ በሆሳዕና ከተማ መክረዋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተመቻቸው የብድር አማራጭ በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረውን ጥረት የሚያግዝ ነው፡፡ በክልሉ ግብርናን በማዘመን የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ቢሆንም የማሽነሪ አቅርቦት ውስንነት እንቅፋት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ባንኩ ለተለያዩ የግብርና ማሽነሪዎች መግዣን ጨምሮ ለአርሶ አደሮች ያመቻቸው የብድር አቅርቦት በዘርፉ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ የተጀመረውን ጥረት ለማጠናከር ያግዛል ነው ያሉት። በግብርና ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ በተጨማሪ የተለያዩ የውሃ አማራጮችን በመጠቀም የወጣቶችን ከዘርፉ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሶላር ሀይል አስፈላጊ መሆኑንም ገልጸዋል። በባንኩ ለግብርናው ዘርፍ የተመቻቸውን የብድር አቅርቦት በአግባቡ መጠቀም የሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ተግባር እንደሚገባም ተናግረዋል።   በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሪቴይል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት ደሳለኝ አለሙ በበኩላቸው እንዳሉት፣ ባንኩ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች ያካተተ የብድር አቅርቦትን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው። አርሶ አደሩም በተሰማራበት የግብርና ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆን የአነስተኛና የረዥም ጊዜ የብድር አቅርቦት መመቻቸቱን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም በዘርፉ የሚመነጨውን ኢኮኖሚ ከማሳደግ በተጨማሪ ዘርፉ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለገበያ ማረጋጋትና መሰል ያሉትን ጠቀሜታዎች ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል። ባንኩ ከአርሶ አደሩ የብድር ፍላጎት ጋር ተያይዞ የሚነሱ የዋስትና ጥያቄ ችግሮችን ለመፍታት ካርታን በዋስትና ማቅረብ የሚቻልበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። በምክክር መድረኩ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አህመድ ሀቢብ እና የክልሉ ህብረት ሥራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ተመስገን ጎዴቦ ተገኝተዋል።
በክልሉ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ፖሊስ የተቀናጀ ተግባር እያከናወነ ነው
Dec 23, 2025 47
ባሕር ዳር፤ ታኅሣሥ 14/2019(ኢዜአ)፡ - በአማራ ክልል ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ፖሊስ ከሌሎች የፍትሕ ተቋማት ጋር የተቀናጀ ተግባር እያከናወነ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ዘላለም መንግስቴ(ዶ/ር) ገለጹ። የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እና የፍትሕ ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ሙስናና ብልሹ አሰራርን የመከላከል ቅንጅታዊ ስራ ላይ የመከረ መድረክ ዛሬ አካሂደዋል።   በመድረኩ የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ዘላለም መንግስቴ(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የክልሉን ሕዝብና መንግስት ሃብት ከምዝበራና ከብልሹ አሰራር ለመታደግ የምርመራና የክስ ተግባር በቅንጅት እየተከናወነ ነው። ፖሊስ በተደራጀ መረጃና ማስረጃ የተደገፈ ምርመራ የማካሄድ ሃላፊነት እንዳለበት ጠቅሰው፤ ሌሎች የፍትሕ ተቋማት ደግሞ በምርመራ የተገኘውን ውጤት ተጠያቂነት እንዲሰፍን የማድረግ ሃላፊነት እንዳለባቸው አንስተዋል። ይህንን የተቋማዊ ቅንጅታዊ አሰራር በማስፋት የተገኘውን አበረታች ውጤት ማጠናከር የሚያስችል ተግባር መቀጠሉን ተናግረዋል። ፖሊስ እና አቃቢ ሕግ መዳረሻቸው ብልሹ አሰራርን መከላከልና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን ማስቻል ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ሃላፊ ብርሃኑ ጎሽም ናቸው።   የቅንጅት ስራው ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህም የተመዘበረ የመንግስትና የሕዝብ ሃብት እንዲመለስ እያስቻለ መሆኑን አንስተዋል። ውስብስብ የሆነውን ሌብነትና ብልሹ አሰራር አስቀድሞ ለመከላከልና ተጠያቂነትን ለማስፈን የቅንጅት ስራው የበለጠ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   ከክልሉ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በኩል የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት የሙስና ወንጀል ችሎት ምርመራ ዋና መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ዳምጤ ባየ፤ ባለፉት አምስት ወራት 556 መዝገቦች ላይ ምርመራ በማከናወን ከእነዚህ ውስጥ የ401 ተጣርቶ ጥፋተኛ በሆኑት ላይ ክስ እንዲመሰረት ለሚመለከተው አካል መላኩን ገልጸዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላችንን እንወጣለን-የመተማ ወረዳ ነዋሪዎች
Dec 23, 2025 38
መተማ፤ ታህሳስ14/2018 (ኢዜአ):-የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ አስተዳደር ነዋሪዎች ተናገሩ። በመተማ ወረዳ ጉባይ ጀጀቢት ከተማ ዘላቂ ሰላም ግንባታን መሰረት ያደረገ ሕዝባዊ ውይይት ዛሬ ተካሄዷል።   በውይይት መድረኩ ላይም ነዋሪዎቹ ፤ የአካቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ሙሉነህ ጥጋቡ ፤ በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም በማፅናት ልማት እንዲጠናከር የሚደግፉ መሆኑን ገልጸዋል። ሕግ የማስከበር ተግባር ተጠናክሮ የሰፈነውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል። ሌላኛው ተሳታፊ አቶ ክፍሌ ለጋስ ፤ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ለሁሉም ነገር ሰላም አስፈላጊ ነው ያሉት ቄስ አሰፋ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ መንግስት ለዘላቂ ሰላም እያደረገ ያለውን ተግባር እንደሚደግፉ አስታውቀዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፤ሕዝቡ በሰላም ማስከበር ተግባር የነቃ ተሳትፎውን ይበልጥ ማጠናከር ይኖርበታል። መንግስት ሰላምን ለማፅናት እያደረገ ያለው የሕግ ማስከበር ተግባር ውጤት እያመጣ መሆኑን አንስተዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረሰ አዱኛ፤ መንግስት ከሕግ ማስከበር ስራ ጎን ለጎን የሰላም አማራጭን ለሚቀበሉ በሆደ ሰፊነት አሁንም በሩን ከፍቷል ብለዋል። ሆኖም በሽፍትነት በመቀጠል ሕዝቡን ሰላም በሚነሱት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ተወያዩ 
Dec 23, 2025 137
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ የኬንያ ፕሬዝደንት ዊልያም ሳሞይ ሩቶን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት መቀበላቸውን ገልጸዋል።   ጉብኝቱ በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጥልቅ፣ ታሪካዊ እና ወንድማዊ ግንኙነት የሚያንፀባርቅ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድ ጋር ተወያዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በብሔራዊ ቤተመንግሥት ይፋዊ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት አድርገዋል በውይይቱ የሁለትዮሽ ግንኙነቱ በሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ መለዋወጣቸውን አመልክተዋል።   ይኽም በሰላም እና መረጋጋት፣ ብሎም በአፍሪካ መር መፍትሔዎች ላይ ያለንን የወል ጽኑ አቋም የሚያሳይ ነበር ሲሉ ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ  ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም  አለባቸው
Dec 22, 2025 134
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ በሥራዎቻቸው ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች የህግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አካሂዷል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የሰላም ግንባታ የእያንዳንዱ ተቋም ኃላፊነት ነው፡፡ ሰላም የሁሉም ዋነኛ አጀንዳ መሆኑን በመግለጽ፤ ሁሉም አካል ሰላምን የእለት ተዕለት እንቅስቃሴው ዕቅድ አካል ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ የሰላም ግንባታ በሁሉም ዕቅዶች፣ በፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መካተት አለበት ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር) ተቋማት ለአዎንታዊ ሰላም (Positive peace) ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡   ተቋማት ግጭትን መከላከልና ማስቀረት የሚያስችል የሰላም ዕቅድ የሥራቸው አካል መሆን አለበት ብለዋል፡፡ በዚህም ከፌደራል እስከ ቀበሌ ያሉ የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡ፣ ሲተገብሩና ክትትል ሲያደርጉ ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Dec 22, 2025 105
ጋምቤላ፤ ታህሳስ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በወቅታዊ የፀጥታና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ ውይይት አድርገዋል።   በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ፤ በክልሉ ሰላምን ለማወክና ልማትን ለማደናቀፍ እኩይ አላማ ይዘው የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸውን ገልጸዋል። በተለይም የፀጥታ ችግር እንዲከሰትና የልማት ስራዎች እንዲስተጓጎሉ ጥረት ማድረጋቸውን አንስተው በህዝቡና የጸጥታ ሃይሉ ትብብር የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰላም የማስጠበቅና ልማትን የማስቀጠል ስራ በልዩ ትኩረት የሚከናወን መሆኑን ተናግረዋል።   በዚህ ጥረት ውስጥ የህዝቡ ትብብር አበረታች መሆኑን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የጥፋት ቡድኖችን እኩይ አላማ በማክሸፍ ለክልሉ ሰላምና ልማት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ተቋማት ሰላምን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለሰላም ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ አለባቸው
Dec 22, 2025 132
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ ተቋማት ሰላምን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለሰላም ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንደሚገባቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች የህግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ እና ሌሎችም የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና እንግዶች ተገኝተዋል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት፤ ሰላም የሁሉም ዋነኛ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የሰላም ግንባታ ጉዳይ በሁሉም ዕቅዶች፣ በፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መካተት ይኖርበታል ብለዋል። ተቋማትም የሰላም ግንባታን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለአዎንታዊ ሰላም (Positive peace) ግንባታ አሻራቸውን አስቀምጠው መሄድ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ ተቋማት የግጭት መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ ጉዳዮችን መከላከልና ማስቀረት በሚያስችል መንገድ መሥራት አለባቸው ብለዋል። እንዲሁም ህግና ስርዓትን ያልተከተሉ አካሄዶችን በማስተካከል፣ የፕሮጀክቶች አፈፃፀምን በማላቅ፣ አሳታፊነትን በማጎልበት ዘላቂና አስተማማኝ ሰላምን ማፅናት እንደሚገባ ተናግረዋል።   የግጭት ጥንስሶችን ከስር መሰረታቸው ለማጥፋት ተጠያቂነትን ማስፈን፣ ስራዎችን በጊዜና በጥራት ማጠናቀቅ ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል። የተቋማት ስራዎች የግጭት መንስኤዎች መሆን የለባቸውም ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር)፤ ግጭትን መከላከልና ሰላም ግንባታ ላይ መሥራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የሰላም ግንባታ በግብርና በጤና እና በሌሎችም ተቋማት እንዴት ይካተት ለሚለው ራሱን የቻለ ሰነድ ሊዘጋጅለት ይገባል ብለዋል።
የሚሰጠንን ሀገራዊ ተልዕኮና ግዳጆች በጀግንነት ለመፈጸም ዝግጁ ነን - ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ አባላት
Dec 22, 2025 182
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ የሀገር ሰላምና የሕዝብ ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚሰጣቸውን ሀገራዊ ተልዕኮ በጀግንነትና በሰብዓዊነት ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ አባላት ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ፖሊስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በፖሊስ አካዳሚው አቅም ያሰለጠናቸውን ልዩ የኮማንዶ ኃይል አባላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በትናንትናው ዕለት በአዋሽ የስልጠና ማዕከል አስመርቋል። ልዩ የኮማንዶ ኃይሉ ልዩ እና አስቸጋሪ ኦፕሬሽኖችን በእውቀትና በጀግንነት የሚፈጽም መሆኑም በዚሁ ወቅት ተጠቁሟል፡፡ ተመራቂ የኮማንዶ አባላቱ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በጀግንነትና በሰብዓዊነት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡   ኮንስታብል ሚኪያስ ገበያው በሰጠው አስተያየት የወሰዱት ስልጠና የአካል ብቃት ብቻ ሳይሆን የአእምሮ ጽናትና ልዩ የኦፕሬሽን ጥበቦችን ያስጨበጣቸው መሆኑን ገልጿል። በዚህም የሚሰጠውን ማንኛውንም ሀገራዊ ተልዕኮ በጀግንነት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ሀገርና ህዝብን ከማንኛውም የጥፋት ኃይል የመጠበቅና የሕዝብን ሰላም ለማስጠበቅ እስከ መስዋዕትነት ጭምር ለመክፈል ዝግጁ መሆኑንም ጠቁሟል፡፡   ሌላኛዋ ተመራቂ ኮንስታብል ምርትነሽ ተካ በሰጠችው አስተያየት የስልጠናው ሂደት ገንቢ፣ አስተማሪና ለቀጣይ ተልዕኮ እንዲዘጋጁ የሚያደርግ መሆኑን ተናግራለች፡፡ ባገኘችው ስልጠና የሚሰጣትን ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኗንም ገልጻለች፡፡ ኮንስታብል አብዲ ተረፈ በበኩሉ ኢትዮጵያን ከውጪ ባዳ እና ከውስጥ ባንዳ ለመጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል፡፡   ቀደምት ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ዳር ድንበር ለማስከበር የፈጸሙትን ገድል በጀግንነት ለመድገም መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የእነሱን ፈለግ በመከተል ሀገራቸውን ለማገልገል መዘጋጀት እንደሚገባቸው ተመራቂዎቹ ጠቁመዋል፡፡ ተመራቂዎቹ ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተውጣጥተው በጋራ ያሳለፉት የስልጠና ጊዜ የኢትዮጵያን አንድነት በተግባር ያዩበት መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኤሊት ፖሊስ ኃይል መገንባቱ የፀጥታ ሪፎርማችን ትልቅ ማሳያ ነው 
Dec 21, 2025 194
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 12/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በተልዕኮው ልዩና ስትራቴጂያዊ የሆነ ኤሊት ፖሊስ ኃይል መገንባቱ የፀጥታ ሪፎርማችን ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ዛሬ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አካዳሚ በራሱ አቅም ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የኮማንዶ ፖሊስ አባላት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በመገኘቴና ይህንን ጀግና የፖሊስ ሠራዊት በመመልከቴ የተሰማኝ ደስታ ላቅ ያለ ነው ብለዋል።   መንግሥታችን በፀጥታ ዘርፉ ባከናወነው መጠነ-ሰፊ ሪፎርም፤ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዛሬ ለሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱ ጠንካራ ዘብ፣ በሙያው ብቁና በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ በሕዝብ ፍቅርና አመኔታ የተገነባ ፕሮፌሽናል ተቋም ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ይህ ኤሊት የፖሊስ ሠራዊት ማንኛውንም ውስብስብና አስቸጋሪ የጸጥታ ስጋቶችን በአጭር ጊዜና በከፍተኛ ብቃት የመቀልበስ ልዩ አቅም እንዳለውም ጠቁመዋል። የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የሕዝባችንን ሰላም የሚፈታተኑ የሽብርና የከባድ ወንጀል ሙከራዎችን በብቃት የመከላከልና መቆጣጠር ኃላፊነት ተጥሎበታል ሲሉም አስታውቀዋል። ሀገራችን በሁሉም መስክ ለምታስመዘግበው ድል ዋነኛው መሠረት ሰላምና ፀጥታ ነው ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመልዕክታቸው።   ለዚህ ሰላም ሲሉ ሕይወታቸውን እስከመስጠት የደረሰ መስዋዕትነት ለከፈሉና ሀገርን ለማጽናት በቁርጠኝነት ለቆሙ የፖሊስ አባሎቻችን ትልቅ ክብር እንደሚገባቸውም ነው ያስገነዘቡት። የእስካሁኑ ስኬት ይበልጥ ለሥራ የሚያተጋ መሆኑንም አመላክተዋል። በመጪው ግንቦት የሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነፃ ሆኖ እንዲከናወን እንደ COP32 ያሉ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ መድረኮች እንዲሁም ደማቅ የአደባባይ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቁ የፌዴራል ፖሊስ ኃይላችን የተጣለበትን ታሪካዊ አደራ በብቃት እንደሚወጣ ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል።   የዛሬ ተመራቂ የኤሊት ፖሊስ ሠራዊት አባላት የኢትዮጵያ ሕዝቦች ኅብረ ብሔራዊ አንድነትና ሉዓላዊነት ምልክት ናችሁ ሲሉም አስረድተዋል። ሀገርንና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከየትኛውም አደጋ የመከላከል ኃላፊነታችሁን በታማኝነት እንድትወጡ አደራ ማለት እፈልጋለሁ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፖለቲካ
የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላችንን እንወጣለን-የመተማ ወረዳ ነዋሪዎች
Dec 23, 2025 38
መተማ፤ ታህሳስ14/2018 (ኢዜአ):-የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ አስተዳደር ነዋሪዎች ተናገሩ። በመተማ ወረዳ ጉባይ ጀጀቢት ከተማ ዘላቂ ሰላም ግንባታን መሰረት ያደረገ ሕዝባዊ ውይይት ዛሬ ተካሄዷል።   በውይይት መድረኩ ላይም ነዋሪዎቹ ፤ የአካቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ሙሉነህ ጥጋቡ ፤ በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም በማፅናት ልማት እንዲጠናከር የሚደግፉ መሆኑን ገልጸዋል። ሕግ የማስከበር ተግባር ተጠናክሮ የሰፈነውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል። ሌላኛው ተሳታፊ አቶ ክፍሌ ለጋስ ፤ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ለሁሉም ነገር ሰላም አስፈላጊ ነው ያሉት ቄስ አሰፋ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ መንግስት ለዘላቂ ሰላም እያደረገ ያለውን ተግባር እንደሚደግፉ አስታውቀዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፤ሕዝቡ በሰላም ማስከበር ተግባር የነቃ ተሳትፎውን ይበልጥ ማጠናከር ይኖርበታል። መንግስት ሰላምን ለማፅናት እያደረገ ያለው የሕግ ማስከበር ተግባር ውጤት እያመጣ መሆኑን አንስተዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረሰ አዱኛ፤ መንግስት ከሕግ ማስከበር ስራ ጎን ለጎን የሰላም አማራጭን ለሚቀበሉ በሆደ ሰፊነት አሁንም በሩን ከፍቷል ብለዋል። ሆኖም በሽፍትነት በመቀጠል ሕዝቡን ሰላም በሚነሱት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ተወያዩ 
Dec 23, 2025 137
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ የኬንያ ፕሬዝደንት ዊልያም ሳሞይ ሩቶን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት መቀበላቸውን ገልጸዋል።   ጉብኝቱ በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጥልቅ፣ ታሪካዊ እና ወንድማዊ ግንኙነት የሚያንፀባርቅ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድ ጋር ተወያዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በብሔራዊ ቤተመንግሥት ይፋዊ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት አድርገዋል በውይይቱ የሁለትዮሽ ግንኙነቱ በሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ መለዋወጣቸውን አመልክተዋል።   ይኽም በሰላም እና መረጋጋት፣ ብሎም በአፍሪካ መር መፍትሔዎች ላይ ያለንን የወል ጽኑ አቋም የሚያሳይ ነበር ሲሉ ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ  ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም  አለባቸው
Dec 22, 2025 134
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡና ሲተገብሩ በሥራዎቻቸው ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች የህግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አካሂዷል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የሰላም ግንባታ የእያንዳንዱ ተቋም ኃላፊነት ነው፡፡ ሰላም የሁሉም ዋነኛ አጀንዳ መሆኑን በመግለጽ፤ ሁሉም አካል ሰላምን የእለት ተዕለት እንቅስቃሴው ዕቅድ አካል ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ የሰላም ግንባታ በሁሉም ዕቅዶች፣ በፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መካተት አለበት ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር) ተቋማት ለአዎንታዊ ሰላም (Positive peace) ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡   ተቋማት ግጭትን መከላከልና ማስቀረት የሚያስችል የሰላም ዕቅድ የሥራቸው አካል መሆን አለበት ብለዋል፡፡ በዚህም ከፌደራል እስከ ቀበሌ ያሉ የመንግሥት ተቋማት ዕቅድ ሲያወጡ፣ ሲተገብሩና ክትትል ሲያደርጉ ከሰላም ግንባታ አንፃር የነበራቸውን ሚና መገምገም እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Dec 22, 2025 105
ጋምቤላ፤ ታህሳስ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በወቅታዊ የፀጥታና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ ውይይት አድርገዋል።   በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ፤ በክልሉ ሰላምን ለማወክና ልማትን ለማደናቀፍ እኩይ አላማ ይዘው የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸውን ገልጸዋል። በተለይም የፀጥታ ችግር እንዲከሰትና የልማት ስራዎች እንዲስተጓጎሉ ጥረት ማድረጋቸውን አንስተው በህዝቡና የጸጥታ ሃይሉ ትብብር የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥና ሰላምን በማጽናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰላም የማስጠበቅና ልማትን የማስቀጠል ስራ በልዩ ትኩረት የሚከናወን መሆኑን ተናግረዋል።   በዚህ ጥረት ውስጥ የህዝቡ ትብብር አበረታች መሆኑን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የጥፋት ቡድኖችን እኩይ አላማ በማክሸፍ ለክልሉ ሰላምና ልማት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ተቋማት ሰላምን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለሰላም ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ አለባቸው
Dec 22, 2025 132
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ ተቋማት ሰላምን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለሰላም ግንባታ አሻራቸውን ማስቀመጥ እንደሚገባቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች የህግ ማውጣት፣ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎች ሲያከናውኑ የሰላም አካቶ ትግበራን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ እና ሌሎችም የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና እንግዶች ተገኝተዋል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት፤ ሰላም የሁሉም ዋነኛ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የሰላም ግንባታ ጉዳይ በሁሉም ዕቅዶች፣ በፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መካተት ይኖርበታል ብለዋል። ተቋማትም የሰላም ግንባታን የዕቅዳቸው አካል በማድረግ ለአዎንታዊ ሰላም (Positive peace) ግንባታ አሻራቸውን አስቀምጠው መሄድ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ ተቋማት የግጭት መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ ጉዳዮችን መከላከልና ማስቀረት በሚያስችል መንገድ መሥራት አለባቸው ብለዋል። እንዲሁም ህግና ስርዓትን ያልተከተሉ አካሄዶችን በማስተካከል፣ የፕሮጀክቶች አፈፃፀምን በማላቅ፣ አሳታፊነትን በማጎልበት ዘላቂና አስተማማኝ ሰላምን ማፅናት እንደሚገባ ተናግረዋል።   የግጭት ጥንስሶችን ከስር መሰረታቸው ለማጥፋት ተጠያቂነትን ማስፈን፣ ስራዎችን በጊዜና በጥራት ማጠናቀቅ ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል። የተቋማት ስራዎች የግጭት መንስኤዎች መሆን የለባቸውም ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር)፤ ግጭትን መከላከልና ሰላም ግንባታ ላይ መሥራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የሰላም ግንባታ በግብርና በጤና እና በሌሎችም ተቋማት እንዴት ይካተት ለሚለው ራሱን የቻለ ሰነድ ሊዘጋጅለት ይገባል ብለዋል።
የሚሰጠንን ሀገራዊ ተልዕኮና ግዳጆች በጀግንነት ለመፈጸም ዝግጁ ነን - ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ አባላት
Dec 22, 2025 182
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ የሀገር ሰላምና የሕዝብ ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚሰጣቸውን ሀገራዊ ተልዕኮ በጀግንነትና በሰብዓዊነት ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን ተመራቂ ልዩ የኮማንዶ አባላት ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ፖሊስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በፖሊስ አካዳሚው አቅም ያሰለጠናቸውን ልዩ የኮማንዶ ኃይል አባላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በትናንትናው ዕለት በአዋሽ የስልጠና ማዕከል አስመርቋል። ልዩ የኮማንዶ ኃይሉ ልዩ እና አስቸጋሪ ኦፕሬሽኖችን በእውቀትና በጀግንነት የሚፈጽም መሆኑም በዚሁ ወቅት ተጠቁሟል፡፡ ተመራቂ የኮማንዶ አባላቱ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በጀግንነትና በሰብዓዊነት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡   ኮንስታብል ሚኪያስ ገበያው በሰጠው አስተያየት የወሰዱት ስልጠና የአካል ብቃት ብቻ ሳይሆን የአእምሮ ጽናትና ልዩ የኦፕሬሽን ጥበቦችን ያስጨበጣቸው መሆኑን ገልጿል። በዚህም የሚሰጠውን ማንኛውንም ሀገራዊ ተልዕኮ በጀግንነት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ሀገርና ህዝብን ከማንኛውም የጥፋት ኃይል የመጠበቅና የሕዝብን ሰላም ለማስጠበቅ እስከ መስዋዕትነት ጭምር ለመክፈል ዝግጁ መሆኑንም ጠቁሟል፡፡   ሌላኛዋ ተመራቂ ኮንስታብል ምርትነሽ ተካ በሰጠችው አስተያየት የስልጠናው ሂደት ገንቢ፣ አስተማሪና ለቀጣይ ተልዕኮ እንዲዘጋጁ የሚያደርግ መሆኑን ተናግራለች፡፡ ባገኘችው ስልጠና የሚሰጣትን ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኗንም ገልጻለች፡፡ ኮንስታብል አብዲ ተረፈ በበኩሉ ኢትዮጵያን ከውጪ ባዳ እና ከውስጥ ባንዳ ለመጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል፡፡   ቀደምት ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ዳር ድንበር ለማስከበር የፈጸሙትን ገድል በጀግንነት ለመድገም መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የእነሱን ፈለግ በመከተል ሀገራቸውን ለማገልገል መዘጋጀት እንደሚገባቸው ተመራቂዎቹ ጠቁመዋል፡፡ ተመራቂዎቹ ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተውጣጥተው በጋራ ያሳለፉት የስልጠና ጊዜ የኢትዮጵያን አንድነት በተግባር ያዩበት መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኤሊት ፖሊስ ኃይል መገንባቱ የፀጥታ ሪፎርማችን ትልቅ ማሳያ ነው 
Dec 21, 2025 194
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 12/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በተልዕኮው ልዩና ስትራቴጂያዊ የሆነ ኤሊት ፖሊስ ኃይል መገንባቱ የፀጥታ ሪፎርማችን ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ዛሬ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አካዳሚ በራሱ አቅም ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የኮማንዶ ፖሊስ አባላት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በመገኘቴና ይህንን ጀግና የፖሊስ ሠራዊት በመመልከቴ የተሰማኝ ደስታ ላቅ ያለ ነው ብለዋል።   መንግሥታችን በፀጥታ ዘርፉ ባከናወነው መጠነ-ሰፊ ሪፎርም፤ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዛሬ ለሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱ ጠንካራ ዘብ፣ በሙያው ብቁና በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ በሕዝብ ፍቅርና አመኔታ የተገነባ ፕሮፌሽናል ተቋም ሆኗል ሲሉም ገልጸዋል። ይህ ኤሊት የፖሊስ ሠራዊት ማንኛውንም ውስብስብና አስቸጋሪ የጸጥታ ስጋቶችን በአጭር ጊዜና በከፍተኛ ብቃት የመቀልበስ ልዩ አቅም እንዳለውም ጠቁመዋል። የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የሕዝባችንን ሰላም የሚፈታተኑ የሽብርና የከባድ ወንጀል ሙከራዎችን በብቃት የመከላከልና መቆጣጠር ኃላፊነት ተጥሎበታል ሲሉም አስታውቀዋል። ሀገራችን በሁሉም መስክ ለምታስመዘግበው ድል ዋነኛው መሠረት ሰላምና ፀጥታ ነው ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመልዕክታቸው።   ለዚህ ሰላም ሲሉ ሕይወታቸውን እስከመስጠት የደረሰ መስዋዕትነት ለከፈሉና ሀገርን ለማጽናት በቁርጠኝነት ለቆሙ የፖሊስ አባሎቻችን ትልቅ ክብር እንደሚገባቸውም ነው ያስገነዘቡት። የእስካሁኑ ስኬት ይበልጥ ለሥራ የሚያተጋ መሆኑንም አመላክተዋል። በመጪው ግንቦት የሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነፃ ሆኖ እንዲከናወን እንደ COP32 ያሉ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ መድረኮች እንዲሁም ደማቅ የአደባባይ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቁ የፌዴራል ፖሊስ ኃይላችን የተጣለበትን ታሪካዊ አደራ በብቃት እንደሚወጣ ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል።   የዛሬ ተመራቂ የኤሊት ፖሊስ ሠራዊት አባላት የኢትዮጵያ ሕዝቦች ኅብረ ብሔራዊ አንድነትና ሉዓላዊነት ምልክት ናችሁ ሲሉም አስረድተዋል። ሀገርንና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከየትኛውም አደጋ የመከላከል ኃላፊነታችሁን በታማኝነት እንድትወጡ አደራ ማለት እፈልጋለሁ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ማህበራዊ
የቱሪስት መስህብ መዳረሻ ሥፍራዎችን የማልማቱ ተግባር ይጠናከራል - ሚኒስቴሩ
Dec 23, 2025 21
ቦንጋ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ተፈጥሯዊና ታሪካዊ የቱሪስት መስህብ መዳረሻ ሥፍራዎችን የማልማቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የቱሪዝም ሚኒስቴር ገለጸ። በሚኒስቴሩ እና ቱር ኢትዮጵያ የተመራ ቡድን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ካፋ ዞን የቱሪስት መዳረሻዎችን ጎብኝቷል። በቱሪዝም ሚኒስቴር የመረጃ ሲነየር ባለሙያ አለማየሁ ወርቅነህ በወቅቱ እንዳሉት፤ እንደሀገር የቱሪዝም ዘርፉን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ አቅም ለማሳደግ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስተዋወቅ በትኩረት እየተሰራ ነው።   በተለይም ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህብ ሥፍራዎችን የማልማቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጠል ገልጸዋል። በዚህ ረገድ በካፋ ዞን በርካታ ተፈጥሯዊና ታሪካዊ የቱሪስት መስህቦች እንደሚገኙ በጉብኝታቸው መመልከታቸውን አንስተዋል። ህብረተሰቡም የተፈጥሮ ምህዳርን ያስጠበቀ ደንን ለቱሪስት መስህብነት ማዋሉ የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተገነቡ የገበታ ለሀገርና ለትውልድ የቱሪስት መዳረሻዎች ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ ማነቃቃታቸውን የገለጹት ደግሞ በክልሉ ባሕል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የማርኬቲንግና ፕሮሞሽን ዳይሬክተር ለምለም አስራት ናቸው። የክልሉን የቱሪስት ሀብቶችን በማስተዋወቅና የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ለማብቃት በቅንጅት መሰራቱን አንስተዋል።   በክልሉ የቱሪስት መዳረሻዎችን፣ በጥናት የመለየት፣ ፓኬጅ የመቅረፅና ማፕ የማዘጋጀት ስራም እንዲሁ። በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የካፋ ዞን ባሕል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ ታሪኳ ታከለ በበኩላቸው፣ በዞኑ 138 ተፈጥሯዊ፣ ታሪካዊና ባህላዊ የቱሪስት መዳረሻዎች መለየታቸውን ተናግረዋል። እነዚህን የቱሪስት መዳረሻዎች በተገቢው ለይቶ ለማልማትና ለማስተዋወቅ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በጉብኝቱ ከተሳተፉ የቱሪዝም ጋዜጠኞች መካከል ዘሪሁን ግርማ፤ ጉብኝቱ የቱሪዝም ሀብቶች ይበልጥ በማስተዋወቅ የዘርፉን ሁለንተናዊ አቅም ለማጎልበት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግሯል። በዚህ ረገድ በካፋ ዞን የቱሪስቶችን ቀልብ የሚስቡ በርካታ መዳረሻዎች እንዳሉ መረዳቱን አንስቷል።  
የጣና ሀይቅ ተፈጥሯዊና ባህላዊ ቅርሶችን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ዝግጅት ተደርጓል
Dec 23, 2025 38
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በጣና ሀይቅ የሚገኙ ተፈጥሯዊና ባህላዊ ቅርሶችን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የአማራ ክልል ባሕል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ። ‎ቢሮው በቅርሶቹ ምዝገባ ዙሪያ ባለድርሻ አካላትን ያካተተ የውይይት መድረክ ዛሬ በባሕርዳር ከተማ አካሄዷል።   በመድረኩ ላይ ‎የቢሮው ምክትል ኃላፊ አየለ አናውጤ (ዶ/ር) እንዳመለከቱት፤ ክልሉ የበርካታ ባህላዊ፣ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶችና ፀጋዎች ባለቤት ነው። ከነዚህም ጣና ሀይቅ ውስጥ የሚገኙት ባህላዊና ተፈጥሯዊ ሃብቶች ጥንታዊ ገዳማቱ፣ አድባራቱና ሌሎች እንደሚገኙ ተናግረዋል። በሀይቁ ውስጥ ያለውን ባህላዊና ተፈጥሯዊ ሃብት በአግባቡ ባለማስተዋወቃችንና ባለመመዝገቡ ከሃብቱ በሚጠበቀው ልክ መጠቀም ሳይቻል እንደቆየ አውስተዋል። ይህንን ለማስተካከልም ባለፉት ሁለት ዓመታት ቢሮው ሀይቁንና በሀይቁ ውስጥ ያለውን ሃብት በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ከፌዴራል መንግሰት የሚመለከተው አካል ጋር ሲያደረግ የቆየው የጥናት ሰነድ ተጠናቆ ለተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ተልኮ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጸዋል። ይህም ቅርሶችን ለዓለም በማስተዋወቅ በርካታ ቱሪስት እንዲጎበኛቸውና ከዘርፉ ክልሉም ሆነ ሀገሪቱ የሚገባቸውን ጥቅም እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።   ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አባ ገብረማርያም ገብረኪዳን በሰጡት አስተያየት እንዳሉት፤ በሀይቁ ውስጥ የሚገኙ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ እየተደረገ ያለው ጥረት ሃብቱን የበለጠ ለማስተዋወቅ የሚያስችል ነው። የባሕርዳርና አካባቢዋ አስጎብኚዎች ማህበር ፀሐፊ አቶ አሰፋ መላክ በበኩላቸው፤ የጣና ሀይቅ ቅርሶች የቱሪስት ፍሰቱን በማሳደግ የአካባቢው ሕብረተሰብና የአስጎብኚ ማህበራትን ይበልጥ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።   በመድረኩ የአስጎብኚ ማህበራት ተወካዮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።  
የመዲናዋ የኮሪደር ልማት የአካል ጉዳተኞችን ደህንነትና ተጠቃሚነት በማስጠበቅ ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል
Dec 23, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የተከናወኑ የኮሪደር እና ሌሎች የልማት ስራዎች የአካል ጉዳተኞችን ደህንነትና ተጠቃሚነት በማስጠበቅ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው ይህንን የገለጸው "አካል ጉዳተኞችን የሚያካትት ማህበረሰብ መገንባት ለተሻለ ማህበራዊ እድገት" በሚል መሪ ሀሳብ ሲከበር የቆየውን ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን በከተማ ደረጃ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ባከበረበት ወቅት ነው።   የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ቆንጂት ደበላ እንደተናገሩት፣ በመዲናዋ የተሰሩ የኮሪደር ልማቶች አካል ጉዳተኞች በመንገዶችና በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚገጥሟቸውን መሰናክሎች በመቅረፍ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። መንገዶች ራሳቸውን የቻሉ ምቹ የአካል ጉዳተኛ መስመር እንዲኖራቸው፣ ተቋማትም የአካል ጉዳተኞች መተላለፊያ መሰረተ ልማቶችን እንዲያሟሉ በማድረግ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን አንስተዋል። አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ ያደረጉ ሌሎች የልማት ሥራዎችም መከናወናቸውን በመጥቀስ፥ በቀጣይም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት አካታች የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በቢሮው የአካል ጉዳተኞች፣ የአረጋውያንና የቤተሰብ ማስተባበሪያ ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት በቀለ በበኩላቸው፣ አካል ጉዳተኞችን በሙያ ስልጠናና በግብዓት በመደገፍ ሰርተው ህይወታቸውን እንዲለውጡ እየተደረገ ነው ብለዋል። የአዲስ አበባ አካል ጉዳተኞች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት ይታጠቁ ደረሰ፣ በመዲናዋ ለአካል ጉዳተኞች ትኩረት ተሰጥቶ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት የሚደነቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።   ለአብነትም መንገድን ጨምሮ ምቹ መሠረተ ልማቶች መገንባታቸውን በማንሳት፥ በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ጠቁመዋል። በማጠቃለያ መድረኩ የእጅ ሥራ ምርቶቻቸውን ያቀረቡ አካል ጉዳተኛ አምራቾች በሰጡት አስተያየት የኮሪደር ልማቱ ለአካል ጉዳተኞች እንቅስቃሴና የሥራ ውጤታማነት ምቹ ምህዳር መፍጠሩን ተናግረዋል። ባገኙት የሙያና የግብዓት ድጋፍ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፥ ይበልጥ ለማሳደግ የመስሪያ ቦታ፣ የገበያ ትስስርና ተከታታይነት ያለው የግብዓት አቅርቦት እንዲኖር ጠይቀዋል።  
መገናኛ ብዙሃን በብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅና አሰባሳቢ ትርክት ግንባታ ላይ ስራዎቻቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Dec 23, 2025 33
ድሬዳዋ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፡- መገናኛ ብዙሃን ብሄራዊ ጥቅምን በማስጠበቅና አሰባሳቢ ትርክትን በመገንባት ረገድ የጀመሯቸውን ስራዎች ይበልጥ አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ። የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ የኢዜአ እና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድሬዳዋ ቅርንጫፎች፣ የኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ቅርንጫፍ እና የምርጫ ቦርድን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውሮ ተመልክቷል። የቋሚ ኮሚቴው አባልና የዘርፉ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ዛራ ቢፍቱ፤ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት(ኢዜአ) እና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን መረጃዎችን ለሕዘብ ተደራሽ በማድረግ የላቀ ሚናቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። የሚዲያ ተቋማቱ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን ከመዘገብ ባለፈ ለብሔራዊ መግባባት፣ ለጋራ ትርክት ግንባታና ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የጀመሯቸውን ስራዎች ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል። የቋሚ ኮሚቴው አባላት በድሬዳዋ የሚገኙትን የኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ቅርንጫፍና የምርጫ ቦርድ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። የዴሞክራሲ ተቋማቱ በጠንካራ አደረጃጀት አቅማቸውን በማጎልበት በኢትዮጵያ የዳበረ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እውን እንዲሆን እያደረጉት ያለውን ጥረት አድንቀዋል። ከጉብኝቱ በኋላም ከድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አብዲ ሙክታር እና ከምክር ቤቱ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል።
ኢኮኖሚ
በባንኩ ለአርሶ አደሩ የተመቻቸው የብድር አማራጭ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዝ ነው - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)
Dec 23, 2025 56
ሆሳዕና፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአርሶ አደሩ ያመቻቸው የብድር አማራጭ በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚያግዝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ባንኩ በግብርናው ዘርፍ አርሶ እና አርብቶ አደሩን ለመደገፍ ባመቻቸው የብድር አማራጭ ላይ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ከባንኩ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ዛሬ በሆሳዕና ከተማ መክረዋል።   ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተመቻቸው የብድር አማራጭ በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረውን ጥረት የሚያግዝ ነው፡፡ በክልሉ ግብርናን በማዘመን የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ቢሆንም የማሽነሪ አቅርቦት ውስንነት እንቅፋት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ባንኩ ለተለያዩ የግብርና ማሽነሪዎች መግዣን ጨምሮ ለአርሶ አደሮች ያመቻቸው የብድር አቅርቦት በዘርፉ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ የተጀመረውን ጥረት ለማጠናከር ያግዛል ነው ያሉት። በግብርና ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ በተጨማሪ የተለያዩ የውሃ አማራጮችን በመጠቀም የወጣቶችን ከዘርፉ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሶላር ሀይል አስፈላጊ መሆኑንም ገልጸዋል። በባንኩ ለግብርናው ዘርፍ የተመቻቸውን የብድር አቅርቦት በአግባቡ መጠቀም የሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ተግባር እንደሚገባም ተናግረዋል።   በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሪቴይል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት ደሳለኝ አለሙ በበኩላቸው እንዳሉት፣ ባንኩ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች ያካተተ የብድር አቅርቦትን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው። አርሶ አደሩም በተሰማራበት የግብርና ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆን የአነስተኛና የረዥም ጊዜ የብድር አቅርቦት መመቻቸቱን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም በዘርፉ የሚመነጨውን ኢኮኖሚ ከማሳደግ በተጨማሪ ዘርፉ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለገበያ ማረጋጋትና መሰል ያሉትን ጠቀሜታዎች ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል። ባንኩ ከአርሶ አደሩ የብድር ፍላጎት ጋር ተያይዞ የሚነሱ የዋስትና ጥያቄ ችግሮችን ለመፍታት ካርታን በዋስትና ማቅረብ የሚቻልበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። በምክክር መድረኩ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አህመድ ሀቢብ እና የክልሉ ህብረት ሥራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ተመስገን ጎዴቦ ተገኝተዋል።
የማዕድን ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚ ያለውን አስተዋፅኦ ይበልጥ ለማሳደግ ቅንጅትን ማጠናከር ወሳኝ ነው
Dec 23, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ የማዕድን ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ ያለውን አስተዋፅኦ ይበልጥ ለማጎልበት ከክልሎች ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሠራር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ ገለጹ። መንግሥት የማዕድን ዘርፉን ከሀገሪቱ አምስት ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ አድርጎ በልዩ ትኩረት እየሠራበት ይገኛል።   ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ በውጭ ምንዛሬ ግኝት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለኢንዱስትሪና ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ግብዓት በመሆን፣ በቴክኖሎጂና መሠረተ ልማት ሽግግር እንዲሁም ገቢን በማሳደግ ረገድ ወሳኝ ሚና አለው። የማዕድን ሚኒስቴር የዘርፉን የሮያሊቲ ገቢ አሰባሰብና አከፋፈልን በተመለከተ ዛሬ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ ከክልል የማዕድን፣ የገንዘብና የገቢዎች ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ምክክር አካሂዷል። የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በዚሁ ወቅት፤ በዘርፉ የሚታዩ የአሠራር ክፍተቶችን ለመሙላትና የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን ግልጽ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በተለይም በሮያሊቲ ገቢ አሰባሰብና አከፋፈል ሂደት ላይ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚነሱ ጉዳዮችን ለማረም ከሚመለከታቸው የክልል ቢሮዎች ጋር በቅርበት እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዛሬው መድረክም ክፍተቶችን ለማስተካከል የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመው፤ ወደ ተግባር ለመቀየርም አስፈላጊው የሕግና የአሠራር እርምጃዎች እንዲወሰዱ ይደረጋል ብለዋል። የማዕድን ዘርፉን ሀገራዊ ሚና ለማላቅም ከክልሎች ጋር ያለው የቅንጅት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰዋል።   በፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ ኃይሉ ኢፋ በበኩላቸው፤ የሮያሊቲ ገቢ አሰባሰብ ላይ ያሉ ክፍተቶችን ለመቅረፍ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች ናቸው ብለዋል። ምክር ቤቱም በሕግ የተቀመጡ አሠራሮች በአግባቡ ተግባራዊ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የማዕድን ሀብት ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ በመሆኑ ለዘርፉ ስኬታማነት በትኩረት እየሠሩ መሆኑን ተናግረዋል። ከሮያሊቲ ገቢ ጋር የተያያዙ ክፍተቶችን በተቀመጠው የሕግ አሠራር መሠረት የማስተካከል ሥራዎችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ የሀገር የህልውና ጉዳይ ሆኖ እየተነሳ ያለ የትውልድ ጥያቄ ነው
Dec 23, 2025 52
መቀሌ ፤ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ የሀገር የህልውና ጉዳይ ሆኖ እየተነሳ ያለ የትውልድ ጥያቄ መሆኑን ምሁራን ገለጹ። በአንድ ወቅት የባህር በር ባለቤት የነበረችው ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር በቅርብ እርቀት ላይ እያለች ምክንያቱ በውል በማይታወቅ መልኩ የባህር መውጫ መግቢያ ተነፍጓት የተቆለፈባት ሀገር ሆናለች። በመሆኑም ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በመልክአ ምድርም ይሁን በዓለም አቀፍ ህግ በቀይ ባህር ላይ መውጫና መግቢያ በር ማጣት የሌለባት በመሆኑ ጉዳዩ አሁን ላይ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ እየተነሳ ይገኛል። የህግና የፖለቲካል ሳይንስ ምሁሩ ያዕቆብ ኃይለማርያም (ዶ/ር) 'አሰብ የማን ናት' በሚለው መፅሃፋቸው የባህር በር ባለቤት በመሆን እና ባለመሆን መካከል ያለውን ልዩነት በስፋት አብራርተዋል። የምጣኔ ሃብት ሊቁን ፖል ኮሊየርን በመጥቀስ 'የባህር በር ከሌለህ ገበያህ የጎረቤት ሃገር ብቻ ነው፤ የባህር በር ካለህ ግን ገበያህ መላው ዓለም ነው' የሚለውን ሃሳብ በማጣቀስ የባህር በር አልባ መሆን ያለውን ጉዳት አስረድተዋል። አሁን ላይ ከ130 ሚሊየን በላይ የሚገመት ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ የባህር በር ሳይኖራት መዝለቅ ማለት ምን ማለት እንደሆነ በቀላሉ መረዳት ይቻላል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የሀገር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚነሳበት ምክንያት ግልጽና የማያሻማ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ በመቀሌ ያነጋገራቸው የማህበራዊና ምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ የሀገር የህልውና ጉዳይ ሆኖ እየተነሳ ያለ የትውልድ ጥያቄ መሆኑን ገልጸዋል። የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያው መዘክር ገብረህይወት፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ተዘግቶባት ልትኖር የማትችል ሀገር መሆኗን አንስተው የባለቤትነት መብቷ ተከብሮ ምላሽ ሊሰጣት ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው ግዙፍ ኢኮኖሚ፣ እያደገ የመጣው የህዝብ ቁጥር እና በቀይ ባህር አካባቢ ያለው ጅኦስትራቴጅክ አስፈላጊነት ታክሎበት ኢትዮጵያ ከባህሩ ተነጥላ ልትኖር የማይገባ መሆኑን አስረድተዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ምላሽ የሚፈልግ የትውልድ ጥያቄ መሆኑን ተናግረዋል።   የምጣኔ ሀብት ባለሙያዋ ሀደራ ባህታ፤ በቀጣናው የምጣኔ ሃብት ትስስርን ማጠናከርና የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ የሚቻለው የአካባቢው አገራት በቀይ ባህር ላይ በጋራ መጠቀም ሲችሉ መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር ያገለለ የትኛውም የልማት እንቅስቃሴ፣ የሰላም ጥረትና ቀጣናዊ ትስስር ትርጉም የሌለው መሆኑን አስረድተዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ከራሷ አልፎ ቀጣናዊ ሰላምና ልማትን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ምላሽ ሊያገኝ ግድ ይላል ብለዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዘላቂ ጥቅም ያስገኛል
Dec 23, 2025 47
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የንግድ ልውውጥ እና የአገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዘላቂ ጥቅም እንደሚያስገኝ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም አሊ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም አሊ የዲጂታል 2030 ስትራቴጂን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የዘመናችን በራሷ የምትተማመን ኢትዮጵያ፣ ብልጽግና በሁሉም ክልሎቿ ለማረጋገጥ የሚያስችል ቁልፍ ስትራቴጂ መሆኑን አመልክተዋል። ስትራቴጂው ለእያንዳንዱ ዜጋ የሚያገለግል፣ አገልግሎት አሰጣጥን የሚያዘምን፣ ኢኮኖሚን የሚያሳድግና እያንዳንዱ ዜጋ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት እንዴት ተሳትፎ ማድረግ እንደሚችል እንደሚያሳይ ተናግረዋል።   ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ያስፈለገው የሰው ሰራሽ አስተውሎት በፍጥነት ማደግ፣ የዜጎች ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት የማግኘት መሻት እና የንግድ ዘርፉ የበለጠ በዲጂታል ዘርፍ መደገፍ ወሳኝ በመሆኑ ምክንያት እንደሆነ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በጀመረችው የዲጂታል ጉዞ በቁርጠኝነት ካልቀጠለች የዲጂታል ክፍፍል እየሰፋ ይመጣል ያሉት አማካሪዋ ስትራቴጂው ያንን ክፍፍል የሚያጠብ እንደሆነ ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አካታች ሉዓላዊ እና በግልጽ አላማ የሚመራ መሆኑንም ነው ጨምረው ያብራሩት። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ መሰረት ጣይ እንደሆነ ገልጸው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የበለጠ ዘርፉን በጥልቀት እንደሚያሰፋ ገልጸዋል። ይህም ከሙከራ ፕሮጀክቶች ወደ ሀገር አቀፍ ስርዓቶችና ከተከፋፈሉ አሰራሮች ወደ ተቀናጁ አገልግሎቶች ለመሸጋገር ያስችላል ነው ያሉት። ሰዎች እና ተቋማትን ማብቃት፣ ሁሉን አቀፍ ዲጂታል ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣ አካታች የኢኮኖሚ እድገት ማፋጠንና ኢትዮጵያ ዋnኛ የዲጂታል መዳረሻ ማድረግ የስትራቴጂው የስኬት መለኪያዎች መሆናቸውን አመልክተዋል።   የኤሌክትሪክ ኃይል፣ ትስስር እና ተአማኒነት የስትራቴጂው ምሰሶዎች መሆናቸውንም ነው ጨምረው አማካሪዋ የገለጹት። በስትራቴጂው አማካኝነት የህዝብ ዲጂታል መሰረተ ልማት የመንግስት አገልግሎቶችን በማዘመንና የዲጂታል አሰራሮችን በማስፋት ዘላቂ የኢኮኖሚ ጠቀሜታን የማስገኘት ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። ከቴክኖሎጂ በተጨማሪ ስትራቴጂው ህጎች፣ መረጃዎች፣ ክህሎት እና ታማኝነት ወሳኝ መሆናቸው በግልጽ መቀመጡን አስረድተዋል። ስትራቴጂው ግብርና፣ ጤና፣ ትምህርት እና ኢንዱስትሪን እንዲሁም ሌሎች ዘርፎችን ያካተተ፣ ሀገር በቀል እና ሰውን ያማከለ እንደሆነም ገልጸዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሃይል እና የኢንተርኔት ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣ የተሻሻለ የህዝብ አገልግሎት መዘርጋት፣ ዳታ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን መስጠት፣ የግል ዘርፍ አቅምን ጠንካራ ማድረግ፣ ለሳይበር ጥቃት በቂ የመከላከል ዝግጁነት መገንባትና ኢትዮጵያን የዲጂታል መሪነት ማጎናጸፍ የስትራቴጂው መዳረሻ ግቦች መሆናቸውን አመልክተዋል። የዲጂታል አማካሪዋ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እንዲሳካ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ትኩረት ተሰጥቶታል
Dec 23, 2025 43
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ሙሉ ለሙሉ ተደራሽ የማድረግ ስራ ይከናወናል ሲሉ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ገለጹ። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። በመርሃ ግብሩ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች ባቀረቡት ማብራሪያ፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ማሳደግ፣ የመንግስት ገቢን መጨመርና የተቀናጀ የመረጃ ስርዓት መዘርጋት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።   የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያሥላሴ፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ ቁልፍ ጉዳይ ሆኖ መተግበሩን አስታውቀዋል። የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ማዳረስ በመንግስት የመቶ በመቶ እቅዶች ውስጥ መካተቱን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት 30 ሚሊየን የሚደርሱ ዜጎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ፋይዳ ትኩረት የተሰጠው በመሆኑ ሙሉ ለሙሉ ተደራሽ የማድረግ ስራ ይከናወናል ብለዋል። በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ሀገራዊ ንቅናቄ በማድረግ 90 ሚሊየን ዜጎችን የፋይዳ መታወቂያ ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን አስታውቀዋል፡፡   የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታዬ ግርማ በበኩላቸው፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂዎች በዜግነት አገልግሎት ላይ ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን ተናግረዋል። ለአብነትም በአዲስ አበባ ከማዕከል እስከ ወረዳ የተዘረጋው የዲጂታል ትስስር ለዚህ ተጠቃሽ ስኬት መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። በሀገር ውስጥ አቅም የለሙ መተግበሪያዎች ለቤተሰብ ምዝገባ፣ ለወሳኝ ኩነትና ለነዋሪዎች አገልግሎት መዋል መጀመራቸውን ገልጸው፤ ይህም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተቋማትን በመረጃ ለማስተሳሰር መሰረት ተጥሏል ነው ያሉት።
በሳይበር ደህንነት ወር የህብረተሰቡን ንቃተ-ህሊና ማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎች ተከናውነዋል
Dec 23, 2025 37
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ በስድስተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር የዜጎችንና የተቋማትን የሳይበር ደህንነት ግንዛቤ ማጎልበት የሚያስችል ስራ መከናወኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ገለጹ። "የሳይበር ደህንነት የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት" በሚል መሪ ሀሳብ ከጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው ስድስተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር የማጠቃለያ እና የእውቅና መርኃ ግብር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ጨምሮ ለሳይበር ደህንንት ወሩ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት እውቅና ተሰጥቷቸዋል።   የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የዘንድሮው የሳይበር ደህንነት ወር በስሉጥ ከተማ ግንባታ እና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭት መከላከል ላይ ያተኮረ እንደነበር ጠቁመዋል። በዚህም አቅምን ከመገንባት አኳያ ትልቅ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው የህበረተሰቡንና የተቋማትን የሳይበር ደህንነት ግንዛቤ ማጎልበት የሚያስችል ስራ መከናወኑን አመላክተዋል። ኢትዮጵያ ብሩህ አዕምሮ ያላቸው ዜጎች ያሏት ሀገር መሆኗን ገልጸው አስተዳደሩ ለባለተሰጥኦ ወጣቶችና ታዳጊዎች ስልጠና በመስጠት እያበቃ እንደሚገኝ ተናግረዋል።   ወሩ ሀገር በቀል እውቀቶችን በስፋት ማስተዋወቅ የተቻለበት መሆኑን አንስተው ወጣቶች ያሏቸውን የሳይበር ደህንነት ክህሎቶች በተለያዩ ውድድሮች ማቅረባቸውን ጠቅሰዋል። በወሩ በአጭር ፊልም ውድድር አንደኛ እና ሁለተኛ የወጡት ዘር አዳም አሰፋ እና አቤነዘር አዲስ በሀሰተኛ መረጃ ስርጭት እና በስልክ የሚፈጸሙ የማጭበርበር ድርጊቶች ዙሪያ የሠሯቸው ፊልሞች ለሽልማት እንዳበቋቸው ተናግረዋል። የተሰጣቸው እውቅና ለላቀ ስኬት የሚያነሳሳ መሆኑን በመጥቀስ፥ በቀጣይ በመሰል ሀገራዊ ሥራዎች ላይ ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስኬት ለዘርፉ ቀጣይ ልማት እና እድገት ጠንካራ መሰረት ጥሏል - የዘርፉ ምሁራን
Dec 23, 2025 42
አዳማ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስኬት በቀጣይም ለዘርፉ ልማት እና እድገት ጠንካራ መሰረት መጣሉን በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሰሞኑን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማጠናቀቂያ እና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት በሰጡት ሰፊ ማብራሪያ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትግበራ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመርሃ ግብሩ ስኬት በብዙ መልኩ የሚገለጽ ስለመሆኑ አንስተው የተቋማት የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ መጠናከር በተለይም ደግሞ የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎት ለዘርፉ ስኬት ጥሩ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ከዚህ በመነሳት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን መፍጠር የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አስረድተዋል። በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ የሚከናወን ሲሆን ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስኬት ዘርፉ ቀጣይ ልማት እና እድገት ጠንካራ መሰረት የጣለ መሆኑን ተናግረዋል።   በዩኒቨርሲቲው የኮምፕዩተር ሳይንስና ኢንጂነሪግ ትምህርት መምህርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ዳይሬክተር ደረጄ ረጋሣ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለዘርፉ እድገት ትልቅ መሰረተ ያኖረ መሆኑን ገልጸዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትግበራ በብዙ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የቴክኖሎጂ እሳቤ እንዲገባ ከማድረግ በዘለለ ህዝቡ ቴክኖሎጂን መጠቀም እንዲጀምር እድል የፈጠረ መሆኑን አብራርተዋል። በተለይም ስትራቴጂው ከቴክኖሎጂ ልማት፣ እድገትና አጠቃቀም አንፃር የተቀመጠውን ግብና ዓላማ ያሳካ እንደነበር አመልክተው ከዲጂታል ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ ከኔትዎርክና ኢንተርኔት ልማት አንጻር የተሰሩ በጎ ስራዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ደግሞ በዘርፉ የተገኘውን መልካም ተሞክሮ በመጠቀም ከቴክኖሎጂ ተደራሽነት ባሻገር በዘርፉ የላቀ ከፍታና እመርታን ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል። ለዚህም አዳዲስ ስልቶችና እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚገባ ጠቅሰው የሰው ኃይሉን በቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ማብቃት፣ ማዋሃድና የህዝቡን ተጠቃሚነት ማስፋት ወሳኝ ነው ብለዋል።   በዩኒቨርሲቲው የኮምፒዩተር ሳይንስና እንጂነሪንግ መምህር፣ የኤሌክትሪካልና ኃይድሮ ኤሌክትሮኒክስ የልህቀት ማእከል አስተባባሪ ከተማ አደሬ(ዶ/ር)፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ዘርፉን ለማሳደግ የሚያግዝ መሰረት የጣለ መሆኑን አመልክተዋል። ስትራቴጂው በሰው ኃይል ልማት፣ በፋይናንስ ሴክተር አገልግሎት እንዲሻሻል፣ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲስፋፋ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነበር ብለዋል። በትራንስፖርት፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በአንድ ማዕከል አገልግሎት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬቶች መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እንዲሳካም የሰው ኃይል አቅም ማጎልበት፣ ቴክኖሎጂውን ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ጋር ማቆራኘት እንዲሁም ፈጣንና ጥራት ያለው የዘርፉ መሰረተ ልማት ዝርጋታ ያስፈልጋል ብለዋል። በዚህ ሂደት የግሉ ዘርፍም አዎንታዊ ሚናውን በሚገባ መጫወት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ስፖርት
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሸገር ከተማን አሸነፈ
Dec 23, 2025 59
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሸገር ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ትዕግስት አዳነ እና ንግስት በቀለ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ገነሜ ወርቁ ለሸገር ከተማ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ውጤቱን ተከትሎ የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ29 ነጥብ ደረጀውን ከአምስተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ አራተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሸገር ከተማ በ27 ነጥብ ከነበረበት አራተኛ ደረጃ ወደ አምስተኛ ዝቅ ብሏል። የቡድኖቹ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ በነበረው ተሳትፎ ምክንያት የተራዘመ ነው። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀሪ ተስተካካይ መርሃ ግብሩን ታህሳስ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከሲዳማ ቡና ጋር እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ዙር ከተስተካካይ መርሃ ግብሮች ውጪ መጠናቀቁ ይታወቃል።
በአፍሪካ ዋንጫ ትኩረት የሳቡ ወጣት ተጫዋቾች
Dec 23, 2025 100
የአፍሪካ ዋንጫ ኮከብ እና አንጋፋ ተጫዋቾች የሚታዩበት መድረክ ብቻ አይደለም። እምቅ ችሎታ እና ብሩህ ተስፋ ያላቸው ወጣት ተጫዎቾች ራሳቸውን የሚያስተዋውቁበትም ጭምር ነው። በተለያዩ የአፍሪካ ዋንጫዎች ደምቀው የታዩ የአፍሪካ ወጣት ተጫዋቾችን ለመመልከት ተችሏል። ጋናዊው አቢዲ ፔሌ፣ የናይጄሪያው ንዋንኮ ካኑ፣ ካሜሮናዊው ሳሙኤል ኤቶ፣ የግብጹ ሆሳም ሚዶ፣ የዛምቢያው ካሉሻ ቡዋሊ፣ ኮትዲቯራዊው ዲዲየር ድሮግባ እና የጋቦኑ ፒዬር-ኤሜሪክ ኦቦሚያንግ በወጣትነት እድሜያቸው በአፍሪካ ዋንጫው ተሳትፎ በማድረግ በቀሪ እግር ኳስ ህይወታቸው ስኬታማ ከሆኑ ተጫዋቾች መካከል ይጠቀሳሉ። 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል። በአፍሪካ ዋንጫው ጎልተው ይታያሉ የተባሉ ተጫዋቾችን እንመልከት። ቢላል ኤል ካኑስ (ሞሮኮ) ኤል ካኑስ በአውሮፓ ከሚጫወቱ የአፍሪካ ተስፈኛ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው። በአሁኑ ሰዓት ከሌይስተር ሲቲ በውሰት ወደ ስቱትጋርት አቅንቶ እየተጫወተ ይገኛል።   በቤልጂየም የተወለደው የ21 ዓመቱ ተጫዋች ለአውሮፓዊቷ ሀገር በታዳጊ ብሄራዊ ቡድኖች በመሰለፍ ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ለሞሮኮ ዋና ቡድን እየተጫወተ ይገኛል። የአጥቂ አማካይ ተጫዋቹ እ.አ.አ በ2022 በኳታር በተካሄደው 22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ሞሮኮ ከክሮሺያ ጋር ባደረገችው የደረጃ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያ ጨዋታውን ለሀገሩ አድርጓል። ከዛ ጊዜ አንስቶ ለሞሮኮ 26 ጨዋታዎችን አድርጎ ሁለት ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። በውስን ቦታዎች እና በጠባብ ክፍቶች መሐል ያለው የፈጠራ አቅም ተጫዋቹ አድናቆት እንዲቸረው አድርጓል። ላሚን ካማራ (ሴኔጋል)   የ21 ላሚን ካማራ የሴኔጋልን ማልያ ለመጀመሪያ ጊዜ የለበሰው እ.አ.አ በ2022 በአልጄሪያ አስተናጋጅነት በተካሄደው ሰባተኛው የአፍሪካ ሀገራት እግር ኳስ ሻምፒዮና (ቻን) ላይ ነው። የሀገር ውስጥ ሊግ ተጫዋቾች ብቻ በሚጫወቱበት ውድድር ከሀገሩ ዋንጫ አንስቷል። በወቅቱ በሩብ ፍጻሜው ሞሪታኒያ ላይ በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ጎል ቡድኑ ለግማሽ ፍጻሜ እንዲያልፍ አስችሎታል። ከዛ ወቅት አንስቶ ለሴኔጋል 34 ጨዋታዎች አድርጎ ስድስት ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። እ.አ.አ በ2024 ከሜትዝ ወደ ሞናኮ በማቅናት እየተጫወተ የሚገኝ ሲሆን በ38 ጨዋታዎች ሁለት ጎሎችን አስቆጥሯል። ለሴኔጋል ዋናው ቡድን በመደበኛነት እየተሰለፈ የሚገኘው ካማራ ከአማካይ ክፍል በመነሳት ወደ ተቃራኒ የግብ ክልል የሚያደርጋቸው ፈጣን ሩጫዎች እና የሚፈጥራቸው የግብ እድሎች አድናቆት እንዲቸረው አድርጓል። ካርሎስ ባሌባ (ካሜሮን)   ካርሎስ ባሌባ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ለብራይተን ኤንድ ሆቭ አልቢየን የሚጫወት ነው። ተጫዋቹ በአማካይ እና በተከላካይ አማካይ ስፍራ መጫወት የሚችል ነው። በካሜሮን ዱዋላ የተወለደው ባሌባ አባቱ ለደቡብ አፍሪካ እና ካሜሮን ክለቦች ተጫውቶ አሳልፏል። እ.አ.አ በ2023 ከፈረንሳዩ ሊል ወደ ብራይተን በማምራት ድንቅ ጊዜን እያሳለፈ ይገኛል። ባሌባ ለካሜሮን የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደረገው እ.አ.አ በ2024 ሀገሩ ከኬፕቨርዴ ጋር ባደረገችው የዓለም ማጣሪያ ጨዋታ ላይ ነው። ከዛ ጊዜ ጀምሮ ለብሄራዊ ቡድኑ 11 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን ምንም ጎል አላስቆጠረም። ታታሪነት፣ ኳስ በብቃት ማንከባለል እና ኳስን ማቀበል የተጫዋቹ መገለጫዎች ናቸው። በሜዳው ውስጥ ከሳጥን እስከ ሳጥን በሚያደርገው እንቅስቃሴ ከፖል ፓግባ፣ ቲያጎ አልካንታራ እና ኬቨን ደ ብሮይን ጋር የሚያነጻጽሩትም አሉ። ኦማር ዲያኪቴ (ኮትዲቭዋር)   የአጥቂ መስመር ተሰላፊው ኦማር ዲያኪቴ በአፍሪካ ዋንጫው ከሚጠበቁ ወጣት ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው። የ21 ዓመቱ ተጫዋች በአሁኑ ከፈረንሳዩ ሬሚስ በውሰት ወደ ቤልጂየሙ ሴርክል ብሩዥ በማምራት እየተጫወተ ይገኛል። ዲያኪቴ ለሀገሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨዋታውን ያደረገው እ.አ.አ በ2023 ኮትዲቭዋር ከሌሴቶ ጋር ባደረገችው ጨዋታ ላይ ሲሆን ለብሄራዊ ቡድኑ ባደረጋቸው 23 ጨዋታዎች ስድስት ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫም ተሳትፎ አድርጓል። የዲያኪቴ የአጨራረስ ብቃት እና የቦታ አያያዙ ለተከላካዮች ፈተና ነው። ትራቪስ ሙታባያ (ዩጋንዳ)   የ20 ዓመቱ ሙታባያ በምስራቅ አፍሪካ እግር ኳስ ተስፋ ከተጣለባቸው ባለ ክህሎት ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው። የአማካይ መስመር ተሰላፊው ከፈረንሳዩ ቦርዶ እ.አ.አ በ2025 ወደ ቱኒዚያው ስፋክሲያን በማምራት እየተጫወተ ይገኛል። በዩጋንዳ ታዳጊ ብሄራዊ ቡድኖች ላይ ድንቅ ብቃቱን ካሳየ በኋላ ከአራት ዓመት በፊት በ16 ዓመቱ በዋናው ቡድን እንዲጫወት ጥሪ ቀርቦለታል። የመጀመሪያ ጨዋታውንም ዩጋንዳ ከታንዛንያ ባደረገችው የወዳጅነት ጨዋታ ላይ አከናውኗል። ለሀገሩ እስከ አሁን ባደረጋቸው 24 ጨዋታዎችን ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎውን የሚያደርገው የ20 ዓመቱ ተጫዋች የመፍጠር አቅሙ፣ የስራ ታታሪነት እና ኳስ የማንከባለል ክህሎቱ አድናቆት እንዲቸረው አድርጓል። የታንዛንያው ኬልቪን ጆን፣ የዛምቢያ ሚጉዌል ቻዋ፣ የሴኔጋሉ ኢብራሂም ምባዬ፣ የሴኔጋሉ ፓፔ ማታር ሳር እና የሞሮኮው ኤሊስ ቤን ሴግሂር ሌሎች አይን ያረፈባቸው ወጣት ተጫዋቾች ናቸው።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ በአንድ ሺህ 52 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው
Dec 23, 2025 50
ደብረ ማርቆስ፤ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን በተያዘው የበጋ ወራት በአንድ ሺህ 52 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ።። በምስራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ባለሙያ አቶ ጤናው አላምረው ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአፈር እና የውሃ ጥበቃ ስራ የአፈር ለምነትን ጠብቆ በማቆየት ለሰብል ምርታማነት ማደግ የጎላ ሚና እያበረከተ ነው። እንዲሁም በተለያየ ምክንያት ተመናምኖ የቆየውን የደን ሃብት መልሶ በመተካት የደን ሽፋኑ ከፍ እንዲል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ይህንኑ ተግባር አጠናክሮ ለማስቀጠልም በዚህ የበጋ ወራት በ1 ሺህ 52 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልፀዋል። በተፋሰሶቹ ከ83 ሺህ 700 ሄክታር በላይ ለምነቱን ያጣ መሬት የሚሸፍን የልማት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራው ከታህሳስ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ሲሆን ለዚሁ የሚሆን የስራ መሳሪያ እና 39 ሺህ ቀያሽ አርሶ አደሮችን በማሰልጠን እንዲሳተፉ እየተደረገ ይገኛል። እስካሁን ስራ በተጀመረባቸው አካባቢዎችም ከአንድ ሺህ 800 ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ ማከናወን ተችሏል ነው ያሉት። የጥራት ደረጃውን ለማስጠበቅና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥም በየደረጃው የሚገኙ የግብርና ባለሙያዎች ለአርሶ አደሮች ሙያዊ እገዛና ድጋፍ እያደረጉ እንደሆነ አስረድተዋል። በአዋበል ወረዳ የጎደና ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ይመኑ መንግስቱ እንዳሉት፤ ቀደም ሲል በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የተከናወነበት ማሳ ለምነቱ በመሻሻሉ በሰብል ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ውጤት አስገኝቷል። ባገኙት ውጤት በመበረታታትም በዚህ የበጋ ወቅት በልማት ቡድን በመደራጀት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራውን እያከናወኑ እንደሚገኝም ገልፀዋል። በዞኑ ባለፈው ዓመት 56 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራ እንደተከናወነ ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻሻለውን የዕፅዋት ጥበቃና ኳራንታይን ረቂቅ አዋጅ አፀደቀ
Dec 23, 2025 102
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የቀረበለትን የተሻሻለውን የዕፅዋት ጥበቃና ኳራንታይን ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ፤ የዕፅዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቂቅ አዋጅ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። ረቂቅ አዋጁም በሰብል ላይ የሚከሰትን የዕፅዋት ተባይ በቅድመ መከላከል የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት የምርት ብክነትን በመቀነስ የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል እንደሚረዳ ገልጸዋል። የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ በዕፅዋትና ብዝኅ ሕይወት ሰፊ ጸጋ ቢኖራትም የተፈጥሮ ሃብቷን በአግባቡ መጠቀም የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ አልነበረም። ይህም ማዕቀፉ ኋላ ቀር የሆነና ለቁጥጥር አመቺ ባለመሆኑ አዋጁን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱ ተገልጿል። ረቂቅ አዋጁ በዕፅዋት ላይ የሚከሰት ተባይና መጤ አረም ምክንያት በግብርና ምርታማነት ላይ የሚደርሰውን ተፅዕኖ በጠንካራ የቁጥጥር ሥርዓት ለመከላከል እንደሚያግዝ አስረድተዋል። የዕጽዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቂቅ አዋጅም የዓለም አቀፍ የዕፅዋት ጥበቃ ስምምነትን መነሻ በማድረግ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ኢትዮጵያ ለዕጽዋት ሀብቶቿ ተገቢውን እንክብካቤ በመስጠት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ አቅም መፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል። የምክር ቤቱ አባላት በዕፅዋት ጥበቃና ኳራንቲን ረቂቅ አዋጅ ላይ ሃሳብና አስተያየት በመስጠት ረቂቅ አዋጁን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት በተወሰኑ የመኸር ሰብል አብቃይ አካባቢዎች አልፎ አልፎ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ሊከሰት ይችላል
Dec 22, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 13/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት በተወሰኑ የመኸር ሰብል አብቃይ አካባቢዎች አልፎ አልፎ ሊከሰት ከሚችል ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታዎች የተሻለ ገጽታ እንደሚኖረው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ። በአብዛኛዎቹ የመኸር ሰብል አብቃይ በሆኑ የሰብል ስብሰባና ድህረ ሰብል ስብሰባ ተግባራት እየተከናወነ በሚገኝባቸው አካባቢዎች ላይ ደረቃማ እርጥበት ሁኔታ እንደሚጠበቅ ገልጿል። በሚቀጥሉት አስር ቀናትም በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ መካከለኛና ሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሰብል ላይ ጉዳይ ሊያስከትል እንደሚችል አስገንዝቧል። ህብረተሰቡም ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሰብል ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ ቅድመ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፏል። በዚህም በደረቅ ቀናት የደረሱ ሰብሎችን መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ጠቁሟል። በተቀሩት የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተስተዋለው ደረቃማ የአየር ሁኔታም የደረሰ ሰብል ለመሰብሰብና ለድኅረ ሰብል ስብሰባ ሥራ አመቺ የአየር ሁኔታ መፍጠሩን አስታውቋል። ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ኢትዮጵያ የሚነፍሰው ደረቅና ቀዝቃዛ የአየር ጠባይ እንደሚቀጥልም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የበጋው ደረቅ፣ ጸሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በአብዛኛዎቹ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚስተዋል ሲሆን የሌሊትና የማለዳው ቅዝቃዜ እንደሚስተዋልም አስገንዝቧል። በዚህም በሰሜን፣ ምስራቅ፣ መካከለኛውና ደቡብ ደጋማ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየስ በታች እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል። ባለፉት ቀናት በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ከነበረው የደመና ሽፋን መጨመር ጋር ተያይዞ በደጋማ አካባቢዎች ላይ የነበረው ቅዝቃዜ እንዲቀንስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደነበረው ገልጿል፡፡
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት ከመገንባት ባለፈ ለብዝሃ ሕይወት መጠበቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው
Dec 20, 2025 180
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እያከናወነች ያለው ተግባር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት ከመገንባት ባለፈ ለብዝሃ ሕይወት መጠበቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ገለጸ። በኢትዮጵያ በየዓመቱ በስፋት የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነትና መሪነት የተጀመረ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ለመመከት፣ የአገሪቷን የደን ሽፋን ለማሳደግና በአረንጓዴ ልማት ላይ የተመሰረተ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያለመ ሲሆን፤ ባለፉት ዓመታት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማሳተፍ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እንዲተከሉ በማድረግ ረገድ ዓለም አቀፍ እውቅናን ያተረፈ ስኬታማ ተግባር ተመዝግቧል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ካርታ ካስኬ (ዶ/ር) እንዳሉት ፤ የአየር ንብረት ለውጥ በብዝሃ ሕይወት ህልውና ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ በማሳደር ለሥነ-ምህዳር መመሰቃቀልና ለዝርያዎች መጥፋት ዋነኛ መንስኤ እየሆነ ይገኛል። ይህንን ስጋት ለመቀነስና የአየር ንብረት ለውጥን ለመመከት የሚከናወኑ ተግባራት ከፍተኛ ለውጥ እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እያከናወነች ያለው የችግኝ ተከላ ተግባር፣ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት እውን ለማድረግ መሠረት እየጣለ መሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የገለጹት። እንደ ካርታ ካስኬ (ዶ/ር) ማብራሪያ፣ የምግብ ሥርዓት ከግብርና ምርታማነትና ከብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ፣ ኢንስቲትዩቱ ይህንን ሥርዓት ለማጠናከር የተለያዩ የአሰራር ስልቶችን ዘርግቶ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል። ለአብነትም የማህበራዊ ዘር ባንኮች ጥምረት አንዱ ሲሆን፤ ይህም በየአካባቢው ያሉና የማይበገር የምግብ ሥርዓትን እውን ማድረግ የሚያስችሉ የሰብል ዝርያዎችን መጠበቅ ያስችላል ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለአካባቢ ጥበቃና ደህንነት መረጋገጥ ትልቅ ማሳያ ተደርጎ እንደሚወሰድ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ይህም የብዝሃ ሕይወት ሀብትን በአግባቡ ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እያገዘው መሆኑን ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጸንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው-ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
Dec 23, 2025 80
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እና ለረጅም ጊዜ ፀንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ኃላፊ አምባሳደር ኮንስታንሲያ አዴሊና ጋስፓራስ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቅርበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት (ዋይት ሃውስ) በተካሄደ ስነ ስርዓት የአምባሳደር ኮንስታንሲያን ሹመት በይፋ ተቀብለዋል። አምባሳደሯ በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ቢሮ ስራቸውን በይፋ ጀምረዋል። ዶናልድ ትራምፕ የአምባሳደር ኮንስታንሲያ የልዑኩ መሪ ሆኖ መመረጥ በጋራ የኢኮኖሚ እድሎች፣ በሉዓላዊ አመራር ሰጪነት እንዲሁም በሰላም እና ደህንነት ላይ የተመሰረተውን የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጽኑ አጋርነት የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በአፍሪካ ሰላም፣ ብልጽግና እና መረጋጋትን ማረጋገጥን ዋና ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የአጋርነት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኝ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት የማጠናከር ፍላጎት አላት -ተሰናባቹ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና
Dec 20, 2025 174
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ሽብርተኝነትን መዋጋትን ጨምሮ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት ለማጎልበት በጋራ መስራቷን እንደምትቀጥል ተሰናባቹ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና ገለጹ። አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ ትብብር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ያለው መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ሀገራቱ የኬንያው የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና መስራች አባት ጆሞ ኬንያታ እና ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ጊዜ አንስቶ ወዳጅነት እንደነበራቸው አውስተው ትብብሩ በከፍተኛ ደረጃ በሚደረጉ ጉብኝቶች እና ውይይቶች እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ጠንካራ አጋርነት ፈጥረው እየሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ጨምሮ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመዋጋት እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ሰላም እና ደህንነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ እና የኬንያ የንግድ ትብብር እያደገ መምጣቱን የገለጹት ተሰናባቹ አምባሳደር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብሩን አድማስ የበለጠ እንደሚያሰፋው ነው የተናገሩት። ቱሪዝም እና ንግድ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ ትስስር እንዲጎለብት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ፣ ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው የ"ላፕሴት ፕሮጀክት" እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ጨምሮ በሌሎች መሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ትስስሩን የሚያሳልጡ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባሳደር ጆርጅ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በማስመረቋ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ግድቡ በቀጣናው ሽግግርን የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1963 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ቀጣናዊ መረጋጋት እና ደህንነት ፣ ንግድ እና የመሰረት ልማት ትስስር የሀገራቱ ዋንጫ የትብብር መስኮች ናቸው።
ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ስለ ህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት ምን አሉ?
Dec 17, 2025 377
የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። በአድዋ ድል መታሰቢያም የአበባ ጉንጉን አኑረዋል። ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ስለ ህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት በስፋት ዘግበውታል። ዓለም አቀፍ የዜና ወኪሎቹ ሮይተርስ እና አሶሲዬትድ ፕሬስ ጉብኝቱን ከ"ጂኦ-ፖለቲካዊ" አንጻር ተመልክተውታል። በተለይ ህንድ በኢትዮጵያ ያላትን የአምስት ቢሊዮን ኢንቨስትመንት አጉልተዋል። አልጀዚራ ትኩረቱን ያደረገው ህንድ በ"ደቡባዊው ዓለም" (Global South) ላይ ያላትን ተጽዕኖ ለማሳደግ በምታደርገው ጥረት ላይ ነው። እንዲሁም የኢትዮጵያና የህንድ ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመካከለኛው ምስራቅና በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ፋይዳም በስፋት አንስቷል። ቢቢሲ እና ፍራንስ 24 ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለየት ያለ አቀባበል ትልቅ የዲፕሎማሲያዊ መቀራረብ ምልክት መሆኑን ዘግበውታል። የአፍሪካ ሚዲያዎች በበኩላቸው የናሬንድራ ሞዲን ጉብኝት "የአፍሪካ-ህንድ" ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ አድርገው ዘግበዋል። አፍሪካ ኒውስ እና ዘ ኢስት አፍሪካን ጉብኝቱ በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መደረጉን በማንሳት፣ ህንድ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ወታደራዊ፣ የጤና እና የቴክኖሎጂ ትብብር እንደሚያጠናክረውም ገልጸዋል። የደቡብ አፍሪካው ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ የናይጄሪያ እና ሌሎች የአፍሪካ መገናኛ ብዙሃን ህንድ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ኢትዮጵያን እንደ መግቢያ በር (Anchor) መጠቀሟን እና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የሚኖረውን ተምሳሌትነት ዘግበዋል። እንደ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ (The Times of India) ፣ ኤንዲቲቪ (NDTV) እና ኤኤንአይ (ANI) ያሉ የህንድ መገናኛ ብዙሃን የሞዲን ጉብኝት ከፍተኛ ሽፋን ሰጥተውታል። የዘገባዎቹ ዋንኛ ትኩረት በኢትዮጵያ ፓርላማ ስላደረጉት ንግግር እና ስለተደረገላቸው ልዩ የክብር ሽልማት ነው። በሌላ በኩልም የዲጂታልና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተደረጉ ስምምነቶችን በዝርዝር አቅርበዋል። አጠቃላይ የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ትኩረት ታሪክ፣ ስትራቴጂካዊ አጋርነት፣ የደቡብ ለደቡብ ትብብር ላይ ያጠነጠኑ ናቸው። የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ መሸጋገሩንም በመገናኛ ብዙሃኑ በስፋት ተነስቷል። ኢትዮጵያ እና ህንድ የተባበሩት መንግስታ ድርጅት እና ብሪክስን ጨምሮ በሌሎች የባለብዙወገን መድረኮች ላይ የደቡባዊውን ዓለም ድምፅ ለማሰማት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸው በዘገባዎቹ በስፋት ተንጸባርቋል።  
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል
Dec 4, 2025 771
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2018(ኢዜአ)፦ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተከናውኗል።   በዕውቅና መርሃ ገብሩ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትአለም መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዘርፍ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ ጋዜጠኝነት፣ ብሮድካስት ሚዲያ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ዘገባዎች እውቅና የሰጠ ነው። በአፍሪካ ሚዲያ ምህዳርን በመቅረጽ ሚናቸውን የተወጡ ጋዜጠኞች ተሸልመዋል። ምርጥ የዜና ዘገባ፣ ምርጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምርጥ ዶክመንተሪ፣ ምርጥ ወቅታዊ ፕሮግራም፣ ምርጥ አፍሪካ ተኮር የመዝናኛ ፕሮግራምና ምርጥ የቪዲዮ ፕሮዳክሽን በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ እና ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው።   አፍሪካ ተኮር ምርጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ምርጥ የወቅታዊ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ እና ምርጥ አጭር የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል የማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። ሁሉም እጩዎች 2000 ዶላር ሽልማት ያገኙ ሲሆን በእያንዳንዱ ዘርፍ ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች የስድስት ሺህ ዶላር ሽልማት አግኝተዋል። የምርጦች ምርጥ የይዘት ፈጣሪዎች አሸናፊም "The Golden Alkebulan" የተሰኘ ልዩ በወርቅ የተለበጠ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በሽልማቱ ላይ ከ40 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ከ800 በላይ ስራዎችን ማቅረባቸውን ተገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ፣ የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽንና የሩስያው አር ቲ ሚዲያ የሽልማቱ አጋር ናቸው።
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 252
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 506
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል።   ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ።   ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡   የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።  
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 832
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል።   የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው።   ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።  
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 1030
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 639
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3092
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 3029
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3929
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 2509
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1611
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7428
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5915
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58642
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53109
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33775
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31305
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26970
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25773
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25329
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25270
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 58642
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53109
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33775
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31305
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ እና የህንድ ዘመን አይሽሬ እና ድንበር  ተሻጋሪ ወዳጅነት 
Dec 16, 2025 396
በሙሴ መለስ (ኢዜአ) ኢትዮጵያ እና ህንድ ረጅም ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አላቸው። በዚህም የስልጣኔ እሴቶችን ይጋራሉ። ሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከፈጠሩ ከ2000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እና ህንድ ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳሽነት እንደሆነም ይወሳል። ኢትዮጵያ እና ህንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1948 ነው። እ.አ.አ በ1950 ሳርዳት ሳንት ሲንግ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያ እና ህንድ በየሀገራቱ ኤምባሲ በመክፈት የዲፕሎማሲ ትብብሩን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ገልጸዋል። ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ እ.አ.አ በ1956 እና በ1958 በህንድ ያደረጓቸው ጉብኝቶች ከኢትዮጵያ መሪዎች ጉብኝቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። እ.አ.አ 1960 ዎቹ ማብቂያ እና 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የህንድ ፕሬዝዳንቶች የነበሩት ሳርቬፓሊ ራድሃክሪሽናን እና ዛኪር ሁሴን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝቶችን አድርገዋል። እ.አ.አ በ2011 ከአንድ ዓመት በፊት ህይታቸው ያለፈው የቀድሞው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንሞሃን ሲንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝትም ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው የህንድ ፕሬዝዳንት ራም ናት ኮቪንድ እ.አ.አ በ2017 የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ በጉብኝታቸው ህንድ እና ኢትዮጵያ በንግድ፣ ኮሙኒኬሽን እና የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 15ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የሀገራቱ መሪዎች በወቅቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ የወጣቶች ክህሎት ማጎልበት እና በሕዝብ ለሕዝብ ልውውጥ ዙሪያ ትብብርን በማጠናከር ዙሪያ ተወያይተዋል። በወቅቱ ህንድ ባዘጋጀችው የሁለተኛው “Voice of Global South Summit” በተሰኘው ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተሳትፎ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲ በህንድ አጠቃላይ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈውም ነበር። የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን የደስታ መግለጫ መልዕክት በመቀበል በአዲሱ የስልጣን ዘመናቸው ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት አጋርነት እንደሚያድግ መግለጻቸውም ይታወሳል። ህንድ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላቸውን አጋርነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። በዚህም ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ትብብር ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥም ነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ያስታወቁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 20ኛው የቡድን 20 አባላት ሀገራት ጉባኤ ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ትርጉም ያለው እና ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ህንድ የቡድን 20 አባል ሀገር መሆኗ የሀገራቱን የባለብዙ ወገን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር ነው። ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ሀገራቱ የሁለትዮሽ እና የባለዙወገን ትብብራቸውን የሚያጠናክሩ ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በወቅቱ የህንድ የትምህርት፣ ንግድ፣ ልማት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የሀገራቱ ግንኙነት የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ድጋፍ ያደረገች ሲሆን በብዝሃ ወገን ማዕቀፉ ሁለቱ ሀገራት በትብብር እየሰሩም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ህንድ በተለያዩ ጊዜያት በአየር ትራንስፖርት፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ መከላከያ፣ ተደራራቢ ታክስን የማስቀረት፣ ንግድ፣ ኮሙኒኬሽን ሳይንስ፣ባህል፣ ትምህርት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መስራት የሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 2025 ኢትዮጵያ እና ህንድ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ የተፈራረሙት የሁለትዮሽ ስምምነት ቁልፍ የሚባል ነው። እ.አ.አ በ2023/24 በወጣ መረጃ የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ምጣኔ 271 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ኢትዮጵያ አተር፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቆዳ ውጤቶች እና የከበሩ ድንጋዮችን ወደ ህንድ ትልካለች። ከህንድ ደግሞ ማሽነሪዎች፣ የመድኃኒትት ምርቶች እና የብረታ ብረት ውጤቶችን በዋናነት ታስገባለች። ህንድ የኢትዮጵያ ዋንኛ የኢንቨስትመንት አጋር ከሚባሉ ሀገራት መካከል ትጠቀሳለች። ከ500 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በጨርቃ ጨርቅ፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ። ህንድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ታደርጋለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ጤና እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከሁለቱ ሀገራት አበይት የትብብር መስኮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ የጉብኝታቸው መርሃ ግብር ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶች እና የጉብኝት ልውውጦች የኢትዮጵያ እና የህንድን ግንኙነት የበለጠ የሚያጸኑ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ህንድ በታዳሽ ኃይል፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ግብርና ማቀነባበሪያን ጨምሮ በአዳዲስ መስኮች ትብብራቸውን የማጠናከር ጽኑ ፍላጎት አላቸው። የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከእርስ በእርስ ግንኙነት ባለፈ የአፍሪካ እና ህንድ እንዲሁም የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። ከ2000 ዓመት በፊት የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ጠንካራ እና ጽኑ ትብብር ተቀይሯል። በማይናወጥ መሰረት ላይም ቆሟል። የበለጠ ጥልቀቱ እየጨመረ የመጣው የሀገራቱ ግንኙነት በጋራ ብልጽግና፣ ስትራቴጂካዊ ትስስር፣ ዘላቂ ልማት እና የሀገራቱን ዜጎች ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ ቁርጠኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።  
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 924
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው።   እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም።   የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል።   የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል።   ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም