ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ማንችስተር ሲቲ ለኤፍኤ ካፕ ፍጻሜ አለፈ
Apr 25, 2026 0
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኤፍኤ ካፕ የመጀመሪያ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ሳውዝሃምፕተንን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በዌምብሌይ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጄሬሚ ዶኩ እና ኒኮ ጎንዛሌዝ ለሲቲ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ፊናን አዛዝ ለሳውዝሃምፕተን ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ ለተከታታይ ዓመት ለኤፍኤ ካፕ ፍጻሜ አልፏል። ሲቲ በፍጻሜው ከቼልሲ እና ሊድስ ዩናይትድ አሸናፊ ጋር ይጫወታል። በሻምፒዮንሺፑ የሚገኘው ሳውዝሃምፕተን ከ23 ዓመታት በኋላ ለኤፍኤ ካፕ ፍጻሜ የማለፍ ህልማቸው አልተሳካም። የኤፍኤ ካፕ ሁለተኛ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በቼልሲ እና ሊድስ ዩናይትድ መካከል ነገ ይካሄዳል።
የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ ነው
Apr 25, 2026 108
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ መሆኑን የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ገለጹ። የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት "የምርጫ ፍትህ በኢትዮጵያ የዳኝነት፣ የፍትሕና የአስተዳደር አካላት ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ የምርምር ኮንፈረንስ አካሂዷል። በዚሁ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ፤ የሕግ ሙያተኞችንና የህብረተሰቡን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የአውደ ጥናት መድረኮች በየጊዜው እንደሚዘጋጁ ገልጸዋል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዳኝነትና የአስተዳደር አካላት የምክክር መድረክም ሂደቱን ፍትሐዊና ሰላማዊ ለማድረግ ተጨማሪ አቅም መሆኑን ተናግረዋል። የምርጫ ዴሞክራሲያዊነትን ለማስጠበቅም የፖሊስ፣ ዓቃቤ ሕግና የፍትሕ ተቋማት ተመጋጋቢ የትብብር ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል። የዜጎች የድምፅ መስጫ ወረቀት ቅቡልነት ያለው መንግስት መመስረቻ ሕጋዊ ኃይል መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሐዊና ቅቡልነት ለማረጋገጥም ህብረተሰቡ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ተቋማት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥራ አመራር አባል አቶ ተክሊት ይመስል፤ በሕገ-መንግስቱና በአዋጅ በተሰጡ ተግባርና ኃላፊነቶች መሠረት የምርጫ ሂደቱ በገለልተኝነት እየተመራ ነው ብለዋል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ለመቋጨትም የሕግና የፍትሕ ተቋማት፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ዜጎችና ባለድርሻ አካላት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ በበኩላቸው ፤ ፖሊስ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝብን ተሳትፎ በማጎልበት የምርጫ ሂደት ሰላማዊነትን የማስጠበቅ ሥራ በብቃት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ለዚህም የምርጫ ቁሳቁስ ደኅንነትን የማስጠበቅና የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከህዝብ ጋር ተከታታይ ውይይቶች እንደሚካሄዱ አስረድተዋል። ከፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ ምትኩ ማዳ ባቀረቡት ፅሁፍ፤ የምርጫ ሂደት ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ ለሕግና ሕገ-መንግስታዊ መርህ ተከባሪነት በትኩረት ይሰራል ብለዋል። ለዚህም በምርጫ ሂደት ተዋናዮች ዘንድ ሊቀርቡ የሚችሉ የሕግና ይግባኝ አቤቱታዎችን አፋጣኝ መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አረጋግጠዋል። በፍትሕ ሚኒስቴር ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ጠገነኝ ትርፌ ባቀረቡት ጽሁፍ፤ ማንኛውም አካል ሕገ-መንግሥቱን የማስከበርና ለሕገ-መንግሥቱ ተገዢ የመሆን ኃላፊነት አለበት ብለዋል። የፍትሕ ሚኒስቴርም ለምርጫ ዓላማ ብቻ ምርመራና ክስ ላይ ለሚሰሩ ዓቃቢያነ ሕግ ስልጠና በመስጠት ግብረ ኃይልና ቡድኖችን በማዋቀር ወደሥራ ማስገባቱን አስረድተዋል።
ባርሴሎና ጌታፌን በማሸነፍ ከሪያል ማድሪድ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 11 ከፍ አደረገ
Apr 25, 2026 108
አዲስ አበባ፤፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በስፔን ላሊጋ የ33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ባርሴሎና ጌታፌን 2 ለ 0 ረትቷል። ማምሻውን በኮሊሲየም ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፌርሚን ሎፔዝ እና ማርከስ ራሽፎርድ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ 28ኛ ድሉን ያስመዘገበው ባርሴሎና በ85 ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። ከተከታዩ ሪያል ማድሪድ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 11 ከፍ አድርጓል። ባርሴሎና የላሊጋውን ዋንጫ ለማንሳት ከቀሪ አምስት ጨዋታዎች የሚፈልገው ስድስት ነጥብ ብቻ ነው። በሊጉ 15ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ጌታፌ በ44 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሪያል ማድሪድ ትናንት ከሪያል ቤቲስ ጋር ባደረገው ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይቷል።
ሊቨርፑል ሲያሸንፍ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከድል ጋር ታርቋል
Apr 25, 2026 86
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 34ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መካሄዳቸውን እንደቀጠሉ ነው። በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሊቨርፑል ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 1 አሸንፏል። አሌክሳንደር ኢሳቅ፣ አንዲ ሮበርተስን እና ፍሎሪያን ዊትዝ ለሊቨርፑል ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ዳንኤል ሙኖዝ ለፓላስ ብቸኛውን ግብ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ሊቨርፑል በ58 ነጥብ ደረጃውን ከአምስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ በማድረግ የአስቶንቪላን ቦታ ተረክቧል። ሻምፒዮንስ ሊግ ለመግባት በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል። ክሪስታል ፓላስ በ43 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። በሞልኒው ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው መርሐ ግብር ቶተንሃም ሆትስፐርስ ዎልቭስን 1 ለ 0 አሸንፏል። ጆአኦ ፓሊንሃ በ82ኛው ደቂቃ ወሳኟን ግብ አስቆጥሯል። ከ15 ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ34 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ላለመውረድ በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። ከሊጉ መውረዱ የተረጋገጠው ዎልቭስ በ17 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ዌስትሃም ዩናይትድ በቶማስ ሱቼክ እና ካሉም ዊልሰን ጎሎች ኤቨርተንን 2 ለ 1 አሸንፏል። ኬርናን ዴውስበሪ-ሆል ለኤቨርተን ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ዌስትሃም ዩናይትድ በ36 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል። ከቶተንሃም ጋር ያለውን የሁለት ነጥብ ልዩነት በማስጠበቅ ላለመውረድ በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። ኤቨርተን በ47 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 102
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
ፖለቲካ
የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ ነው
Apr 25, 2026 108
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ መሆኑን የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ገለጹ። የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት "የምርጫ ፍትህ በኢትዮጵያ የዳኝነት፣ የፍትሕና የአስተዳደር አካላት ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ የምርምር ኮንፈረንስ አካሂዷል። በዚሁ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ፤ የሕግ ሙያተኞችንና የህብረተሰቡን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የአውደ ጥናት መድረኮች በየጊዜው እንደሚዘጋጁ ገልጸዋል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዳኝነትና የአስተዳደር አካላት የምክክር መድረክም ሂደቱን ፍትሐዊና ሰላማዊ ለማድረግ ተጨማሪ አቅም መሆኑን ተናግረዋል። የምርጫ ዴሞክራሲያዊነትን ለማስጠበቅም የፖሊስ፣ ዓቃቤ ሕግና የፍትሕ ተቋማት ተመጋጋቢ የትብብር ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል። የዜጎች የድምፅ መስጫ ወረቀት ቅቡልነት ያለው መንግስት መመስረቻ ሕጋዊ ኃይል መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሐዊና ቅቡልነት ለማረጋገጥም ህብረተሰቡ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ተቋማት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥራ አመራር አባል አቶ ተክሊት ይመስል፤ በሕገ-መንግስቱና በአዋጅ በተሰጡ ተግባርና ኃላፊነቶች መሠረት የምርጫ ሂደቱ በገለልተኝነት እየተመራ ነው ብለዋል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ለመቋጨትም የሕግና የፍትሕ ተቋማት፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ዜጎችና ባለድርሻ አካላት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ በበኩላቸው ፤ ፖሊስ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝብን ተሳትፎ በማጎልበት የምርጫ ሂደት ሰላማዊነትን የማስጠበቅ ሥራ በብቃት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ለዚህም የምርጫ ቁሳቁስ ደኅንነትን የማስጠበቅና የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከህዝብ ጋር ተከታታይ ውይይቶች እንደሚካሄዱ አስረድተዋል። ከፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ ምትኩ ማዳ ባቀረቡት ፅሁፍ፤ የምርጫ ሂደት ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ ለሕግና ሕገ-መንግስታዊ መርህ ተከባሪነት በትኩረት ይሰራል ብለዋል። ለዚህም በምርጫ ሂደት ተዋናዮች ዘንድ ሊቀርቡ የሚችሉ የሕግና ይግባኝ አቤቱታዎችን አፋጣኝ መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አረጋግጠዋል። በፍትሕ ሚኒስቴር ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ጠገነኝ ትርፌ ባቀረቡት ጽሁፍ፤ ማንኛውም አካል ሕገ-መንግሥቱን የማስከበርና ለሕገ-መንግሥቱ ተገዢ የመሆን ኃላፊነት አለበት ብለዋል። የፍትሕ ሚኒስቴርም ለምርጫ ዓላማ ብቻ ምርመራና ክስ ላይ ለሚሰሩ ዓቃቢያነ ሕግ ስልጠና በመስጠት ግብረ ኃይልና ቡድኖችን በማዋቀር ወደሥራ ማስገባቱን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉትን የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን ሸኝተናል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Apr 25, 2026 718
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉትን የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን ሸኝተናል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የፕሬዝደንቱ የኢትዮጵያ ቆይታ በሁለትዮሽ የጋራ አጀንዳዎች ላይ ውይይት የተካሄደበት እና በተለያዩ ዘርፎች ስምምነት የተደረሰበት ፍሬያማ ቆይታ ነበር ብለዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ ዋናውን ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻው ዝግጅት እየተከናወነ ይገኛል
Apr 25, 2026 452
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክሩ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተጠናቅቆ ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻው ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። በኢትዮጵያ ለዘመናት ሲንከባለሉ የቆዩ የልዩነት ሀሳቦችን በምክክር ለመፍታትና በሃሳብ የበላይነት የሚያምን ትውልድ ለመፍጠር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አዲስ ምዕራፍ ጀምሯል፡፡ ኮሚሽኑ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራን ያከናወነ ሲሆን ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን የመለየት ሥራ በስኬት አጠናቅቋል። ኮሚሽኑ የተሳታፊዎች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት፣ ከወረዳ ጀምሮ እስከ ክልሎችና ማዕከል ድረስ በግልጸኝነት የተካሄደ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ በዚህም ኮሚሽኑ ወደ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ምዕራፍ ለመሸጋገር የሚያስችለውን አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። ኮሚሽኑ እስካሁን ያከናወናቸው ተግባራት፣ ኢትዮጵያዊያን በውስጣዊ ጉዳዮቻቸው ላይ በነጻነት መክረው ዘላቂ ሰላምና ብሔራዊ መግባባት እንዲሰፍን የሚያስችል ታሪካዊ ዕድል የፈጠሩ መሆናቸው ይታመናል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለዘላቂ ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሰረት የሚጥል ነው፡፡ ምክክሩ ዜጎች በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች መግባባት ላይ በመድረስ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ዘላቂ ልማትና ዕድገት ማስመዝገብ የሚችሉበትን ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ የሀሳብ ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ በንግግር መፍታት ወሳኝ ነው ያሉት ዋና ኮሚሽነሩ፤ ዜጎች በሀገራዊ ምክክሩ የተፈጠረውን ዕድል በመጠቀም ለሀገራቸው ሰላምና ልማት ገንቢ ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በምክክር ሂደቱ በክልላቸውና በሀገራቸው ያሉ ችግሮችን ነቅሰው በማውጣት ለኮሚሽኑ ማቅረባቸውን አስታውሰዋል፡፡ በሁሉም ክልሎች፣ በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር መካሄዱንም ጠቅሰዋል፡፡ በቀጣይ ሳምንታት በሀገር አቀፍ ደረጃ 170 ለሚደርሱ የተመረጡ አማካሪዎች ስልጠና እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡ በሀገራዊ ምክክሩ ጉባኤ የሚሳተፉ ዜጎች ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል የሚወክሉ መሆናቸውን በማንሳት፤ ዋና ጉባኤውን ለማካሄድም የመጨረሻ ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ፣ እንደ ሀገር በማያግባቡ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር ረገድ በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ ይታወቃል።
ችግሮችን በምክክር በመፍታት የጋራ ሀገርን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ሚናችንን እናጠናክራለን
Apr 25, 2026 398
ወልቂጤ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ችግሮችን በምክክር በመፍታት የጋራ ሀገርን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ሚናችንን እናጠናክራለን ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን ገለጹ። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) ፤ ሀገራዊ ምክክር ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ ዩኒቨርሲቲው ለሂደቱ ስኬታማነት ጥናታዊ ጽሁፎችን በማዘጋጀትና የውይይት መድረኮችን በማመቻቸት ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መፍትሄ መሆኑን በመጥቀስ፣ ሀገራዊ አንድነትን ለማምጣት ያለውን ፋይዳ ለማሳካት ዩኒቨርስቲው አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ ከበደ ገለታ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እያከናወነ ያለው ተግባር ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ቀዳሚው አማራጭ መሆኑን ገልጸዋል። ተነጋግሮ እና ተመካክሮ እልባት ላይ መድረስ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መረጋጋትን ያመጣል፤ ይህም በዜጎች መካከል የጋራ መተማመንን ይፈጥራል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም የኮሚሽኑ የሥራ ዘመን መራዘሙ ይበልጥ አሳታፊ እና የጠራ ሥራ ለማከናወን ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ በምክክር ምዕራፎቹ ስኬት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላው የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህር ኢንጂነር ቀነኒ ኤልያስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አለመግባባቶችን በውይይት የመፍታት ባህል እንዲዳብር ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን የምክክሩን ስኬታማነት የሚያግዙ ጥረቶችን እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ለምክክሩ ሂደት ስኬታማነት ህዝቡ የሚያደርግው በጎ አስተዋጽኦ ውጤት እንዲያመጣ በተለይ ደግሞ የዘርፉ ምሁራን ሚና ትልቅ ነው ብለዋል። የቆዩና የማያግባቡ ችግሮች ላይ በጋራ በመምከር ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር የሚደረገው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን የሁሉም ጥረት ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ መምህር ስለሺ ታመነ (ዶ/ር) ናቸው። ይህ ሂደት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማሳያ መሆኑን በመጥቀስ፣ በምርምር የተደገፈ ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የክልሉን ህዝብ የሰላምና የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራትን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል
Apr 25, 2026 256
ባህርዳር፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ የክልሉን ህዝብ የሰላም እና የልማት ተግባራት ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለፁ። ''አርቆ ማየት አልቆ መስራት'' በሚል መሪ ሃሳብ የክልሉ ያለፉት ዘጠኝ ወራት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ በባህር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በመድረኩ እንደገለፁት፤ በክልሉ የሚከናወኑ ሁሉም ተግባራት ከዚህ ቀደም ከነበረው የአሰራር ሂደት በተለየ ሁኔታ፣ በልዩ ትኩረትና በተሻለ መንገድ መፈፀም ይገባል። በተለይም በክልሉ ሰላምን በተቀናጀ አግባብ ከማስከበር ባሻገር ህዝብ በየደረጃው የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዘላቂነት የመፍታት ስራ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት። የክልሉን ህዝብ የሰላሙም ሆነ የልማቱ ግንባር ቀደም ተሳታፊና ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራትን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል ብለዋል። እንዲሁም ነባራዊ ሁኔታውን ታሳቢ በማድረግና በመረዳት አመራሩ ሁሉን አቀፍ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሔደው የግምገማ መድረክ የተገኙ ስኬቶችን ከማስቀጠል ባለፈ በአፈፃፀም ወቅት የታዩ እንከኖችን በጥልቀት በማየት በቀሪ ወራት በጊዜ የለኝም መንፈስ እንዲፈፀሙ የሚያደርግ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም አመላክተዋል። በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ በበኩላቸው፤ በክልሉ ባለፋት ወራት ዘላቂ ሰላምን መገንባት የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት በቅንጅት ተከናውነዋል ብለዋል። እንዲሁም ጠንካራ አመራር በመስጠት የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውንም አስረድተዋል። በየዘርፋ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በቀጣይ በላቀ ስኬት ማከናወን እንዲቻል አመራሩ በትኩረት ስራዎችን ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። በመድረኩ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች እየተሳተፉ ሲሆን የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎም ይጠበቃል።
የምርጫ ፍትህ መረጋገጥ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ መሰረት ነው
Apr 25, 2026 319
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ የምርጫ ፍትህ መረጋገጥ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ መሰረት መሆኑን የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ገለጹ። የምርጫ ፍትህን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል። የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት "የምርጫ ፍትህ (Electoral Justice) በኢትዮጵያ የዳኝነት፣ የፍትህ እና የአስተዳደር አካላት ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው የምርምር ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ በየወሩ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት የሕግ ባለሙያዎችና የህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲዳብር በስፋት እየሠራ ይገኛል። የምርጫ ፍትህ ርዕሰ ጉዳይ የተመረጠው የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መሠረት በመሆኑ ነው ብለዋል። በሀገራችን ለሰባተኛ ጊዜ ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ባለበት በዚህ ወቅት የምርጫ ፍትህ ላይ መምከር ወቅታዊና አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ዴሞክራሲን እንደ አንድ የተሳሰረ ሥርዓት መመልከት እንደሚገባና በዚህ ሂደት ውስጥ የምርጫ ቦርድ፣ የፖሊስ፣ የዓቃቤ ሕግና የፍትህ አካላት ሚና የማይነጣጠል መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የምርጫ ሂደት ስኬታማ እንዲሆን ተቋማት ብቻ ሳይሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ የበኩሉን ሚና መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲት ጋር ተወያዩ
Apr 24, 2026 1863
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲት ጋር ቀጣናውን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት፤ የሁለቱን ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ መለዋወጣቸውን ገልጸዋል፡፡ እንዲሁም የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም አስፍረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል
Apr 24, 2026 1408
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ከሰአት በኋላ የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት፤ ይኽ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ እና ዘላቂ ግንኙነት የሚያሳይ መሆኑን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው ፤ትብብራችንን እና የጋራ ፍላጎቶቻችን ለማጠናከር የሚያስችል ፍሬያማ ውይይት እንደምናደርግ እምነቴ ነውም ብለዋል።
ፖለቲካ
የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ ነው
Apr 25, 2026 108
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የምርጫ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ መሆኑን የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ገለጹ። የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት "የምርጫ ፍትህ በኢትዮጵያ የዳኝነት፣ የፍትሕና የአስተዳደር አካላት ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ የምርምር ኮንፈረንስ አካሂዷል። በዚሁ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ፤ የሕግ ሙያተኞችንና የህብረተሰቡን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የአውደ ጥናት መድረኮች በየጊዜው እንደሚዘጋጁ ገልጸዋል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዳኝነትና የአስተዳደር አካላት የምክክር መድረክም ሂደቱን ፍትሐዊና ሰላማዊ ለማድረግ ተጨማሪ አቅም መሆኑን ተናግረዋል። የምርጫ ዴሞክራሲያዊነትን ለማስጠበቅም የፖሊስ፣ ዓቃቤ ሕግና የፍትሕ ተቋማት ተመጋጋቢ የትብብር ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል። የዜጎች የድምፅ መስጫ ወረቀት ቅቡልነት ያለው መንግስት መመስረቻ ሕጋዊ ኃይል መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሐዊና ቅቡልነት ለማረጋገጥም ህብረተሰቡ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ተቋማት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥራ አመራር አባል አቶ ተክሊት ይመስል፤ በሕገ-መንግስቱና በአዋጅ በተሰጡ ተግባርና ኃላፊነቶች መሠረት የምርጫ ሂደቱ በገለልተኝነት እየተመራ ነው ብለዋል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ለመቋጨትም የሕግና የፍትሕ ተቋማት፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ዜጎችና ባለድርሻ አካላት ገንቢ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ በበኩላቸው ፤ ፖሊስ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝብን ተሳትፎ በማጎልበት የምርጫ ሂደት ሰላማዊነትን የማስጠበቅ ሥራ በብቃት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ለዚህም የምርጫ ቁሳቁስ ደኅንነትን የማስጠበቅና የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከህዝብ ጋር ተከታታይ ውይይቶች እንደሚካሄዱ አስረድተዋል። ከፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ ምትኩ ማዳ ባቀረቡት ፅሁፍ፤ የምርጫ ሂደት ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ ለሕግና ሕገ-መንግስታዊ መርህ ተከባሪነት በትኩረት ይሰራል ብለዋል። ለዚህም በምርጫ ሂደት ተዋናዮች ዘንድ ሊቀርቡ የሚችሉ የሕግና ይግባኝ አቤቱታዎችን አፋጣኝ መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አረጋግጠዋል። በፍትሕ ሚኒስቴር ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ጠገነኝ ትርፌ ባቀረቡት ጽሁፍ፤ ማንኛውም አካል ሕገ-መንግሥቱን የማስከበርና ለሕገ-መንግሥቱ ተገዢ የመሆን ኃላፊነት አለበት ብለዋል። የፍትሕ ሚኒስቴርም ለምርጫ ዓላማ ብቻ ምርመራና ክስ ላይ ለሚሰሩ ዓቃቢያነ ሕግ ስልጠና በመስጠት ግብረ ኃይልና ቡድኖችን በማዋቀር ወደሥራ ማስገባቱን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉትን የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን ሸኝተናል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Apr 25, 2026 718
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉትን የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን ሸኝተናል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የፕሬዝደንቱ የኢትዮጵያ ቆይታ በሁለትዮሽ የጋራ አጀንዳዎች ላይ ውይይት የተካሄደበት እና በተለያዩ ዘርፎች ስምምነት የተደረሰበት ፍሬያማ ቆይታ ነበር ብለዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ ዋናውን ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻው ዝግጅት እየተከናወነ ይገኛል
Apr 25, 2026 452
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ ምክክሩ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተጠናቅቆ ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻው ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። በኢትዮጵያ ለዘመናት ሲንከባለሉ የቆዩ የልዩነት ሀሳቦችን በምክክር ለመፍታትና በሃሳብ የበላይነት የሚያምን ትውልድ ለመፍጠር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አዲስ ምዕራፍ ጀምሯል፡፡ ኮሚሽኑ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራን ያከናወነ ሲሆን ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን የመለየት ሥራ በስኬት አጠናቅቋል። ኮሚሽኑ የተሳታፊዎች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት፣ ከወረዳ ጀምሮ እስከ ክልሎችና ማዕከል ድረስ በግልጸኝነት የተካሄደ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ በዚህም ኮሚሽኑ ወደ ዋናው ሀገራዊ የምክክር ምዕራፍ ለመሸጋገር የሚያስችለውን አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። ኮሚሽኑ እስካሁን ያከናወናቸው ተግባራት፣ ኢትዮጵያዊያን በውስጣዊ ጉዳዮቻቸው ላይ በነጻነት መክረው ዘላቂ ሰላምና ብሔራዊ መግባባት እንዲሰፍን የሚያስችል ታሪካዊ ዕድል የፈጠሩ መሆናቸው ይታመናል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለዘላቂ ሰላምና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሰረት የሚጥል ነው፡፡ ምክክሩ ዜጎች በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች መግባባት ላይ በመድረስ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ዘላቂ ልማትና ዕድገት ማስመዝገብ የሚችሉበትን ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ የሀሳብ ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ በንግግር መፍታት ወሳኝ ነው ያሉት ዋና ኮሚሽነሩ፤ ዜጎች በሀገራዊ ምክክሩ የተፈጠረውን ዕድል በመጠቀም ለሀገራቸው ሰላምና ልማት ገንቢ ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በምክክር ሂደቱ በክልላቸውና በሀገራቸው ያሉ ችግሮችን ነቅሰው በማውጣት ለኮሚሽኑ ማቅረባቸውን አስታውሰዋል፡፡ በሁሉም ክልሎች፣ በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር መካሄዱንም ጠቅሰዋል፡፡ በቀጣይ ሳምንታት በሀገር አቀፍ ደረጃ 170 ለሚደርሱ የተመረጡ አማካሪዎች ስልጠና እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡ በሀገራዊ ምክክሩ ጉባኤ የሚሳተፉ ዜጎች ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል የሚወክሉ መሆናቸውን በማንሳት፤ ዋና ጉባኤውን ለማካሄድም የመጨረሻ ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ፣ እንደ ሀገር በማያግባቡ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር ረገድ በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ ይታወቃል።
ችግሮችን በምክክር በመፍታት የጋራ ሀገርን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ሚናችንን እናጠናክራለን
Apr 25, 2026 398
ወልቂጤ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ችግሮችን በምክክር በመፍታት የጋራ ሀገርን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ሚናችንን እናጠናክራለን ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን ገለጹ። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) ፤ ሀገራዊ ምክክር ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ ዩኒቨርሲቲው ለሂደቱ ስኬታማነት ጥናታዊ ጽሁፎችን በማዘጋጀትና የውይይት መድረኮችን በማመቻቸት ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መፍትሄ መሆኑን በመጥቀስ፣ ሀገራዊ አንድነትን ለማምጣት ያለውን ፋይዳ ለማሳካት ዩኒቨርስቲው አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ ከበደ ገለታ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እያከናወነ ያለው ተግባር ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ቀዳሚው አማራጭ መሆኑን ገልጸዋል። ተነጋግሮ እና ተመካክሮ እልባት ላይ መድረስ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መረጋጋትን ያመጣል፤ ይህም በዜጎች መካከል የጋራ መተማመንን ይፈጥራል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም የኮሚሽኑ የሥራ ዘመን መራዘሙ ይበልጥ አሳታፊ እና የጠራ ሥራ ለማከናወን ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ በምክክር ምዕራፎቹ ስኬት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላው የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህር ኢንጂነር ቀነኒ ኤልያስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አለመግባባቶችን በውይይት የመፍታት ባህል እንዲዳብር ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን የምክክሩን ስኬታማነት የሚያግዙ ጥረቶችን እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ለምክክሩ ሂደት ስኬታማነት ህዝቡ የሚያደርግው በጎ አስተዋጽኦ ውጤት እንዲያመጣ በተለይ ደግሞ የዘርፉ ምሁራን ሚና ትልቅ ነው ብለዋል። የቆዩና የማያግባቡ ችግሮች ላይ በጋራ በመምከር ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር የሚደረገው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን የሁሉም ጥረት ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ መምህር ስለሺ ታመነ (ዶ/ር) ናቸው። ይህ ሂደት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማሳያ መሆኑን በመጥቀስ፣ በምርምር የተደገፈ ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የክልሉን ህዝብ የሰላምና የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራትን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል
Apr 25, 2026 256
ባህርዳር፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ የክልሉን ህዝብ የሰላም እና የልማት ተግባራት ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለፁ። ''አርቆ ማየት አልቆ መስራት'' በሚል መሪ ሃሳብ የክልሉ ያለፉት ዘጠኝ ወራት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ በባህር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በመድረኩ እንደገለፁት፤ በክልሉ የሚከናወኑ ሁሉም ተግባራት ከዚህ ቀደም ከነበረው የአሰራር ሂደት በተለየ ሁኔታ፣ በልዩ ትኩረትና በተሻለ መንገድ መፈፀም ይገባል። በተለይም በክልሉ ሰላምን በተቀናጀ አግባብ ከማስከበር ባሻገር ህዝብ በየደረጃው የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በዘላቂነት የመፍታት ስራ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት። የክልሉን ህዝብ የሰላሙም ሆነ የልማቱ ግንባር ቀደም ተሳታፊና ተጠቃሚ የማድረግ ተግባራትን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ማከናወን ይገባል ብለዋል። እንዲሁም ነባራዊ ሁኔታውን ታሳቢ በማድረግና በመረዳት አመራሩ ሁሉን አቀፍ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ለሁለት ቀናት በሚካሔደው የግምገማ መድረክ የተገኙ ስኬቶችን ከማስቀጠል ባለፈ በአፈፃፀም ወቅት የታዩ እንከኖችን በጥልቀት በማየት በቀሪ ወራት በጊዜ የለኝም መንፈስ እንዲፈፀሙ የሚያደርግ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም አመላክተዋል። በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ በበኩላቸው፤ በክልሉ ባለፋት ወራት ዘላቂ ሰላምን መገንባት የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት በቅንጅት ተከናውነዋል ብለዋል። እንዲሁም ጠንካራ አመራር በመስጠት የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውንም አስረድተዋል። በየዘርፋ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በቀጣይ በላቀ ስኬት ማከናወን እንዲቻል አመራሩ በትኩረት ስራዎችን ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። በመድረኩ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች እየተሳተፉ ሲሆን የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎም ይጠበቃል።
የምርጫ ፍትህ መረጋገጥ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ መሰረት ነው
Apr 25, 2026 319
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ የምርጫ ፍትህ መረጋገጥ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ መሰረት መሆኑን የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ገለጹ። የምርጫ ፍትህን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የተቋማት ሚና ወሳኝ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል። የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት "የምርጫ ፍትህ (Electoral Justice) በኢትዮጵያ የዳኝነት፣ የፍትህ እና የአስተዳደር አካላት ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው የምርምር ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ በየወሩ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት የሕግ ባለሙያዎችና የህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲዳብር በስፋት እየሠራ ይገኛል። የምርጫ ፍትህ ርዕሰ ጉዳይ የተመረጠው የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መሠረት በመሆኑ ነው ብለዋል። በሀገራችን ለሰባተኛ ጊዜ ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ባለበት በዚህ ወቅት የምርጫ ፍትህ ላይ መምከር ወቅታዊና አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ዴሞክራሲን እንደ አንድ የተሳሰረ ሥርዓት መመልከት እንደሚገባና በዚህ ሂደት ውስጥ የምርጫ ቦርድ፣ የፖሊስ፣ የዓቃቤ ሕግና የፍትህ አካላት ሚና የማይነጣጠል መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የምርጫ ሂደት ስኬታማ እንዲሆን ተቋማት ብቻ ሳይሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ የበኩሉን ሚና መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲት ጋር ተወያዩ
Apr 24, 2026 1863
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲት ጋር ቀጣናውን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት፤ የሁለቱን ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ መለዋወጣቸውን ገልጸዋል፡፡ እንዲሁም የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም አስፍረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል
Apr 24, 2026 1408
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ከሰአት በኋላ የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት፤ ይኽ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ እና ዘላቂ ግንኙነት የሚያሳይ መሆኑን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው ፤ትብብራችንን እና የጋራ ፍላጎቶቻችን ለማጠናከር የሚያስችል ፍሬያማ ውይይት እንደምናደርግ እምነቴ ነውም ብለዋል።
ማህበራዊ
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 102
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
የግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ለማዘመን ጉልህ ድርሻ እየተወጡ ነው
Apr 25, 2026 212
ሮቤ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የወጣቶችን የሥራ ፈጣሪነት ክህሎት ከማሳደግ ባሻገር የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ለማዘመን ጉልህ ድርሻ እየተወጡ መሆኑ ተመላከተ። የአጋርፋ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ በተለያዩ ሙያዎች በደረጃ 4 ያሰለጠናቸውን 592 ተማሪዎችን አስመርቋል። ተማሪዎቹ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ፣ በእጽዋት ሳይንስ፣ በእንስሳት ሳይንስ፣ በመሬት አስተዳደርና ልማት ዘርፍ የተመረቁ መሆናቸውም ተመልክቷል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) እንዳሉት በለውጡ ዓመታት የክህሎት ልማትንና የቴክኒክና ሙያ ዘርፍን ለማጠናከር በተሰሩ ሥራዎች አበረታች ለውጦች ታይተዋል። በዚህም ተግባራዊ የተደረጉ ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃዎች ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህል እንዲነቃቃ አስችሏል ብለዋል። በተለይ በግብርናው ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ የሚያሰለጥኑ የግብርና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የወጣቶችን የሥራ ፈጣሪነት ክህሎት ከማሳደግ ባሻገር የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ለማዘመን ጉልህ ድርሻ እየተወጡ መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪም ዘመናዊ የመሬት አስተዳደር ልማትን ተደራሽ በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች እንዲፈቱ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥሩም አስረድተዋል። የአጋርፋ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅም የዚሁ አንዱ ማሳያና በዘርፉ የተማረ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ አይነተኛ ሚና እየተወጣ ያለ አንጋፋ ተቋም መሆኑንም አክለዋል። ተመራቂዎችም በኮሌጁ ቆይታቸው ያገኙትን የንድፈ ሀሳብ ዕውቀት በአካባቢያቸው ከሚገኙ ፀጋዎች ጋር በማቀናጀት በተማሩት ሙያ አርሶና አርብቶ አደሩን በቅንነት እንዲያገለግሉ አስገንዝበዋል። የአጋርፋ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሌጅ ዲን አቶ ፍራኦል ኢደኦ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኮሌጁ የግብርና ክፍለ ኢኮኖሚውን ለማዘመን በዘርፉ የተማረ የሰው ኃይል የማፍራት ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው። በተለይ በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በጥናትና ምርምር እንዲፈቱ ለማስቻል በዘርፉ የተመረቁ ሰልጣኞች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን አክለዋል። ኮሌጁ ከመማር ማስተማሩ ተግባር በተጓዳኝ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ምርምሮችና የማህበረሰብ አገልግሎቶችን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሬት አስተዳደርና ልማት ዘርፍ የተመረቀው ፉአድ ሲራጅ፤ በኮሌጁ የትምህርት ቆይታው ያገኘውን ዕውቀት ለማህበረሰብ አገልግሎት ለማዋል ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል። ተማሪ አቤል አዱኛ በበኩሉ፤ በተለይ በተፈጥሮ ሃብት ልማት ዘርፍ በአገሪቱ የተጀመሩ ውጤታማ ሥራዎች ይበልጥ እንዲጠናከሩ የበኩሌን እወጣለሁ ብሏል። በምረቃ መርሐግብሩ በትምህርታቸው ብልጫ ላስመዘገቡ ተማሪዎች የሜዳሊያና የዋንጫ ሽልማት በዕለቱ የክብር እንግዶች ተበርክቷል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ ወባን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በተሰሩ ስራዎች ስርጭቱን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ተችሏል
Apr 25, 2026 138
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ የወባ በሽታን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በተከናወኑ የተለያዩ ተግባራት ስርጭቱን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ እንደተቻለ ጤና ሚኒስቴር ገለጸ። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር በበኩላቸው በአስተዳደሩ ወባን ለመከላከል በተሰሩ ስራዎች የተገኙ ውጤቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየተሰራ ነው ብለዋል። አለም አቀፍ የወባ ቀን "ወባን ለማጥፋት እንነሳ፤ አሁንም እንችላለን" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች ዛሬ በድሬዳዋ ተከብሯል። በስነ-ስርዓቱ የተገኙት በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ህይወት ሰለሞን እንደገለፁት፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ወባን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በተሰሩ ስራዎች ስርጭቱን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ተችሏል። የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በ560 ወረዳዎች እና በ12 ሺህ 260 ቀበሌዎች በተከናወኑ ሰፊ እና የተቀናጁ ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን አንስተዋል። ለወባ በሽታ መንስኤ የሆኑ የትንኝ መራቢያ ስፍራዎችን በማፋሰስና በማድረቅ፣ ከ16 ሚሊየን በላይ ዘመናዊ አጎበሮችን ለተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች በማሰራጨት ከ32 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎችን ጤና መጠበቅ መቻሉን ገልፀዋል። በተጨማሪም ከ2 ሚሊየን በላይ ተጋላጭ ቤቶች ፀረ-ትንኝ ኬሚካል ርጭት በማካሄድ የተሰሩ ስራዎች የወባ ስርጭትን 46 በመቶ መቀነስ አስችለዋል ብለዋል። የስርጭቱ መጠን ከቦታ ቦታ ቢለያይም የወባ በሽታን በተሻለ ቅንጅት መከላከል መቻሉን ጠቅሰው ከ5 ሚሊየን በላይ በወባ ለተያዙ ዜጎች ተገቢውን ህክምና በመስጠት ማዳን መቻሉንም ዶክተር ህይወት ጠቅሰዋል። እነዚህን ውጤታማ ተግባራት ለማሳደግ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የወባ መከላከያ ክትባት በ58 ወረዳዎች መጀመሩን ጠቅሰው ክትባቱ በተለይ የህፃናትና እናቶችን ጤና ለመጠበቅ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አመልክተዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር በበኩላቸው በአስተዳደሩ ወባን ለመከላከል በተሰሩ ስራዎች የተገኙ ውጤቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከንቲባው አክለውም፤ ወባን የመከላከልና የማጥፋት ስራ ለአንድ ሴክተር ብቻ የሚተው አለመሆኑን በመገንዘብ ጤናማ ማህበረሰብን የመፍጠር ጉዞን በውጤት መደምደም ይገባል ብለዋል። ህብረተሰቡም የወባ ትንኝ መራቢያ ስፍራዎችን በማፋሰስ፣ የአካባቢውንና የቤቱን ንፅህና በመጠበቅ እያበረከተ ያለውን አስተዋፅኦ ማጠናከር እንዳለበትም አሳስበዋል። በአስተዳደሩ የወባ በሽታ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የመጨመር አዝማሚያ ቢያሳይም በተከናወኑ የተቀናጁ የመከላከል ስራዎች የበሽታውን ስርጭት መቀነስ ተችሏል ያሉት ደግሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፅጌረዳ ክፍሌ ናቸው። በአስተዳደሩ ወባ እና በወባ ንክሻ የሚተላለፉትን የደንጊና የቹኩንጊኒያ በሽታዎች ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውንም አክለዋል። በስነ-ስርዓቱ የፌደራልና የክልሎች የዘርፉ አመራሮች፣ የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች፣ ተማሪዎች፣ በየደረጃው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ ሆነዋል።
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤት ተመዝግቧል
Apr 25, 2026 99
አዳማ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤት መመዝገቡን የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቢሮ ገለፀ። የቢሮው የበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀምና የቀጣይ አምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ የውይይት መድረክ በአዳማ ገልመ አባገዳ አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጉዮ ዋሪዮ እንደገለፁት፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተደረገ ጥረት ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ አበረታች ውጤት ተመዝግቧል። በዚህም የደንበኞች የፍትህ አገልግሎት ዕርካታ ከመጨመሩም ባለፈ የክስ መዝገቦችን በማጥራትና በወቅቱ ውሳኔ እንዲያገኙ በማድረግ ስኬታማ ስራዎችን ለማከናወን ተችሏል። በዚህም ለሌብነት፣ ለብልሹ አሰራርና ለአገልግሎት ጥራት መጓደል በር የሚከፍቱ አሰራሮችን ማስወገድ የተቻለ መሆኑንም ነው የተናገሩት። በዚሁ ወቅት በተከናወኑት ተግባራትም በፍትህ አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ሊኖር የሚችለውን የህብረተሰቡን ቅሬታ መፍታት መቻሉንም አስረድተዋል። ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤት የተገኘ ቢሆንም የክስ መዝገቦች ጥራት ላይ ያሉ ክፍተቶችን ለመሙላት አሰራሩን የማዘመን ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል። አሰራሩን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ አገልግሎት ለመስጠትም የተለያዩ መተግበሪያዎች ለምተው ወደ ስራ እየገቡ መሆኑንም አብራርተዋል። የአርሲ ዞን አቃቤ ህግ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከማል አብዳ በበኩላቸው፤ በዞኑ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተደረገው ጥረት ውጤት የተገኘበት እንደሆነም አንስተዋል። በተለይ በዞኑ ሴቶች፣ ህፃናትና አረጋውያንን ጨምሮ 433 መዝገቦች በነፃ የህግ ውሳኔ እንዲያገኙ በማድረግ ሁለንተናዊ የፍትህ ተደራሽነትን በማረጋገጥ ረገድ የተሻለ አፈፃፀም መመዝገቡንም አክለዋል። ቢሮው ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተለያዩ አካላት እጅ የነበረን ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ያስመለሰ ሲሆን በመንግሥት ላይ የቀረቡ ክሶችን ተከራክሮ በመርታት ከመንግስት ካዝና ይወጣ የነበረን ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ መታደጉንም ገልጿል።
ኢኮኖሚ
የፋብሪካዎቹ ምርቃት ሁለንተናዊ እድገት ዕውን ለማድረግ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል
Apr 25, 2026 223
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተመረቁት ፋብሪካዎች ዘላቂ፣ የማይበገር እና ሁለንተናዊ እድገትን ለማረጋገጥ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነቡትን አራት ግዙፍ ፋብሪካዎችን በይፋ መርቀዋል። የተመረቁት ፋብሪካዎች የቶዮ ሶላር ኢነርጂ ምዕራፍ ሁለት፣ የኦሪጂን እና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎችን እንዲሁም የኤች.ዜድ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካን ያካተቱ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የሶላር ፋብሪካዎቹ በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹሕ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን፣ የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካ ደግሞ በዓመት 900 ቶን ኦክስጅን፣ 40,000 ቶን ናይትሮጅን እና 7 ቶን ሃይድሮጅን ለገበያ ያቀርባል። ይህ ክንውን የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ለማፋጠን፣ የኢነርጂ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም ዘላቂ፣ የማይበገር እና ሁለንተናዊ እድገትን ዕውን ለማድረግ የተቀረጸውን ስትራቴጂ በማሳካት ረገድ ትልቅ ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰድ ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገኙ ፋብሪካዎችን መረቁ
Apr 25, 2026 149
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሲዳማ ክልል ሐዋሳ ከተማ በሚገኘው የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ አራት ከፍተኛ የማምረት አቅም ያላቸው ፋብሪካዎች ዛሬ መርቀው ከፍተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገኙት የቶዮ ሶላር ኢነርጅ ሁለተኛው ምዕራፍ፣ ኦርጅን እና ሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎችን እንዲሁም የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካዎች መመረቃቸውን ገልጸዋል። የሶላር መሠረተ ልማቶቹ በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋዋት ንጹህ ኃይል የሚያመነጩ ሲሆን፤ የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካ ደግሞ በዓመት 900 ቶን ኦክስጅን፣ 40,000 ቶን ናይትሮጅን እና 7 ቶን ሃይድሮጅን እንደሚያቀርቡ አመልክተዋል። አራቱ ፕሮጀክቶች ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር እና የብዙዎችን ኑሮ መደገፍ መቻላቸውንና ከፍተኛ የማምረት ዐቅም ያላቸው ፋብሪካዎቹ የኢትዮጵያም እምቅ ሐብት ወደ ጥቅም የቀየሩም ሆነዋል ብለዋል።
በክልሉ በግብርናው ዘርፍ የምርት እድገት ለማስመዝገብ በርብርብ መስራት ይገባል- ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር)
Apr 25, 2026 84
ባህርዳር ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በግብርናው ዘርፍ የሚጠበቀውን የምርት እድገት ለማስመዝገብ በየደረጃው ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ገለጹ። ቢሮው የ2018/2019 የመኸር ሰብል ልማት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በባህርዳር ከተማ አካሂዷል። የገጠር ክላስተር አስተባባሪው ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በመጭው የመኸር ምርት ወቅት የአርሶ አደሩን የምግብ ሉአላዊነትን የሚያረጋግጥና ለገበያ የሚተርፍ ምርት ማምረት ይጠበቃል። ለዚህም አርሶ አደሩን በልማት ቡድን አደራጅቶ ወደ ሰብል ልማቱ በማስገባትና ከልማዳዊ አሰራር በማላቀቅ በአዳዲስ እሳቤዎች ላይ የተመሰረተ አመራረት ዘይቤን መከተል እንደሚገባ ገልጸዋል። በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያም አርሶ አደሩ ዘመኑ የደረሰበትን የማምረት እውቅትን እንዲጨብጥ በማድረግ ስራ ላይ በማተኮር ለምርት እድገቱ ስኬት በቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ይህም የግብርና ኤክስቴንሽንን በተሟላ በመተግበር፣ በሜካናይዜሽን ላይ በማተኮር፣ በኩታገጠምና የኮንትራት ፋርሚንግ አሰራርን በማስፈን ከምግብ በዘለለ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። "ያልተደራጀ ባለሙያና አርሶ አደር ምርታማነትን ማረጋገጥ አይችልም" ያሉት ዶክተር ድረስ አርሶ አደሩ በተደረጃ አግባብ በሰብል ልማቱ ላይ እንዲረባረብ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቃልኪዳን ሽፈራው በበኩላቸው በመጭው የመኸር ወቅት በዘር ከሚሸፈነው 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ 70 በመቶውን በገበያ ተፈላጊ የሆኑ ሰብሎች ለመሸፈን እየተሰራ ነው። ምርታማነትን ለማሳደግም ግብዓትና ቴክኖሎጂን በአግባቡ ከመጠቀም ባሻገር የተጠናከረ የአረምና የተባይ ቁጥጥር ስራን ለማከናወን አቅጣጫ ተቀምጦ ከወዲሁ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በክልል ደረጃ የተጀመረውን የንቅናቄ መድረክ በቀጣይ እስከ ታች ድረስ ለሚገኘው ባለሙያና አርሶ አደር በማውረድ መግባባት ይፈጠራል ብለዋል፡፡ በንቅናቄ መድረኩ ላይ ከክልልና ከምዕራብ አማራ ከሚገኙ ዞኖች የተውጣጡ የግብርና አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የኢትዮጵያን የስፖርት ሃብቶች አዕምሯዊ መብት ባለቤትነት በማረጋገጥ ለገፅታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት መጠቀም ያስፈልጋል
Apr 25, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የስፖርት ዘርፍ ሃብቶች አዕምሯዊ መብት ጥበቃ ባለቤትነት በማረጋገጥ ለገፅታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት መጠቀም እንደሚያስፈልግ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ገለጸ። የዓለም አዕምሯዊ ንብረት ቀን ''አዕምሯዊ ንብረትና ስፖርት፡ እንዘጋጅ፣ እንጀምር፣ እንፍጠር” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ሁነቶች በአዲስ አበባ ተከብሯል። በዝግጅቱ በስፖርት ዘርፍ የሚጠበቁ የአዕምሯዊ ንብረት መብቶችን ለህዝብ ዕይታ በማቅረብ የፈጠራና ስፖርት ሃብቶችን ጥቅም ላይ ማዋል በሚያስችሉ አጀንዳዎች ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል። በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አማካሪ ፎዚያ አሚን(ዶ/ር)፤ በስፖርት ዘርፍ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ መሠረተ ልማቶች እየተገነቡ ነው ብለዋል። የስፖርት ሁነቶች ከውድድር መድረክነት ባሻገር ከሀገር ስምና ዝና፣ ፋሽን፣ ዲዛይንና ከመገናኛ ብዙኅን ስርጭት ጋር የተቆራኙ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም የስፖርት ተወዳዳሪዎች የግልና የጋራ ፈጠራ፣ ንድፍና የመልካም ዝና ታሪኮችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ባለድርሻ አካላትም የስፖርት ሃብቶችን አዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ በማረጋገጥ ለሀገር ገፅታ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዘርፉ ተዋናዮች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ገንቢ ሚና ሊወጡ ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያን ምርትና አገልግሎቶች በዓለም ንግድ ሥርዓት ለማሳለፍ በሚደረገው ሰፊ ዝግጅትም የስፖርት ዘርፍ አዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ሥርዓትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመስል በበኩላቸው፤ የስፖርት ዘርፍ አዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ የአትሌቶችን ዓለምአቀፍ ዕውቅና ለማላቅ ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል። ለዚህም የኢትዮጵያን ስምና ዝና በዓለም መድረክ ያስጠሩ አትሌቶችን የግልና የጋራ ድል አዕምሯዊ መብት ጥበቃ እንዲደረግላቸው ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የዓለም አዕምሯዊ ንብረት ቀንም የባለድርሻ አካላትን ግንዛቤ በማሳደግ የስፖርት ሃብቶችን አዕምሯዊ ንብረት ባለቤትነት ጥበቃ ለማረጋገጥ እንደሚረዳ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የስፖርት ዘርፍ ሃብቶችን አዕምሯዊ መብት ጥበቃ ማረጋገጥ ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ በኢትዮ-አሊያንስ አድቮኬሲ የአእምሯዊ ንብረትና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ደሱ (ዶ/ር) ናቸው። የስፖርት ቤተሰቡም የአትሌቲክስና የተለያዩ የስፖርት ዘርፍ ሃብቶችን ሕጋዊ ዕውቅና በማስገኘት የአዕምሯዊ መብት ጥበቃ ምዝገባ ማደረግ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትና አላስፈላጊ ወጪን አስቀርቶልናል - ተገልጋዮች
Apr 25, 2026 95
ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልት እና ያልተገባ ወጪን እንዳስቀረላቸው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ከተማ ተገልጋዮች ገለፁ፡፡ በማዕከሉ አገልግሎት በማግኘት ላይ የነበሩት አቶ ዮናስ ሴራሞ ለኢዜአ እንደገለፁት ፤የገቢ ግብር ጉዳይ ላይ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ማዕከሉ እንደመጡና ባጠረ ጊዜም የሚፈልጉትን ፈጽመው ለመመለስ መቻላቸውን ነው የሚገልጹት። የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተገልጋይን ከአላስፈላጊ ከሆነ እንግልትና ወጪ እንደሚታደግ በተግባር ያረጋገጡ መሆኑንም ተናግረዋል። የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ለማውጣት ወደ ማዕከሉ የመጣው ወጣት ሞላልኝ ታምራት በወቅቱ አገልግሎቱን ማግኘቱን እና ማዕከሉ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ይታይ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር በመቅረፍ ለማሕበረሰቡ አስፈላጊ የሆነ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ነው የገለጸው። በማዕከሉ የተገልጋዩን ክብር የጠበቀ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኝቷ እንዳስደሰታት የምትገልፀው ደግሞ ወጣት በረከት ዱቲሶ ናት፡፡ በፋይዳ መታወቂያዋ ላይ ያጋጠማትን የስም ስህተት በአጭር ጊዜ ማስተካከል ችያለሁ ብላለች። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ከበደ ሻሜቦ ማዕከሉ በስምንት ተቋማት 27 አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ እስካሁን ድረስ ከ 20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠት መቻሉንም አስረድተዋል፡፡ በከተሞች በመሬት ዘርፍ የሚሰጡና ለብልሹ አሰራር ተጋላጭ የሆኑ አዳዲስ 48 አገልግሎቶች ተለይተዉ በማዕከሉ ውስጥ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻልም ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል፡፡
ተማሪዎች ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን እንዲያፈልቁ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል
Apr 25, 2026 111
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ ተማሪዎች ችግር ፈቺና ተወዳዳሪ የፈጠራ ስራዎችን እንዲያፈልቁ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን የከተማው ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ገለጹ። ቢሮው “በሳይንስና ፈጠራ የተካነ ትውልድ ለተምሳሌታዊ ሀገር” በሚል መሪ ሐሳብ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየው 11ኛው የሳይንስና የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ተጠናቋል። በአውደ ርዕዩም በተማሪዎችና መምህራን የቀረቡ የፈጠራ ሀሳቦች ተወዳድረው የላቀ ውጤት ላመጡ ተሳታፊዎች የሽልማት አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ተከናውኗል። የቢሮው ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ተማሪዎች ከቀለም ትምህርት ጎን ለጎን የፈጠራ ክህሎታቸውን አውጥተው እንዲጠቀሙ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በየዓመቱ የሚዘጋጀው ይህ የሳይንስና የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይም ተማሪዎችና መምህራን ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡና የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልፀዋል። ውድድሩ ተማሪዎችን በምርምርና በስልጠና በማገዝ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለመቅረፅ ያለመ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፤ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን በተግባር እንዲከውኑና ወደ ሳይንሳዊ ግኝት እንዲቀይሩ ትልቅ አቅም መፈጠሩን አስረድተዋል። በዘንድሮው አውደ ርዕይ ላይ ወደ 3 ሺህ 7 መቶ የሚጠጉ የፈጠራ ስራዎች ለውድድር መቅረባቸውን ጠቅሰው ከእነዚህም ውስጥ ከፍተኛ ውጤት ላመጡ አሸናፊዎች የእውቅና ሽልማት ተበርክቷል ብለዋል። መድረኩ ከውድድር ባለፈ ለብዙዎች የተሻለ ነገን በተስፋ ለመጠበቅ መሠረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመው፣ ለዚህም ስኬት ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ገልፀዋል። ከአውደ ርዕዩ ተሳታፊዎች መካከል የኢትዮ-ጃፓን 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሃብታሙ ደምስ ፤ለእርሻ አገልግሎት የሚውልና በፀሐይ ሃይል የሚሰራ ትራክተር በመስራት በውድድሩ የ1ኛ ደረጃ አሸናፊ ሆኗል። ተማሪ ሃብታሙ ፤ አርሶ አደሩ ከባህላዊ የእርሻ ዘዴ ተላቆ በቴክኖሎጂ ታግዞ እንዲያመርት ለማስቻል መሣሪያውን እንደሰራ ገልጿል። በተመሳሳይ የቡርቃ ዋዮ ትምህርት ቤት ተማሪ ፌኔት በንቲ፤ በስዕልና ቅርፃቅርፅ የፈጠራ ስራ ተወዳድራ የ2ኛ ደረጃ አሸናፊ መሆን ችላለች። ተሳታፊ ተማሪዎቹ እንደገለጹት፤ መሰል አውደ ርዕዮች ያላቸውን እምቅ አቅም አውጥተው እንዲጠቀሙና ከሌሎች ተማሪዎች ልምድ እንዲቀስሙ ትልቅ እገዛ እያደረገላቸው ይገኛል።
መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ፈጣን እና ጊዜ ቆጣቢ ነው- ተገልጋዮች
Apr 24, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ወደ እኛ ከመቅረቡም ባለፈ ፈጣን እና ጊዜ ቆጣቢ ሆኖ አግኝተነዋል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ የታመነበትን መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በይፋ መርቀው ሥራ ማስጀመራቸው ይታወቃል። በምረቃው ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፤ ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም ዜጎች ጊዜ ቆጣቢ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል በቁርጠኝነት እየተሠራ ይገኛል። የመሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት አጭር ጊዜ ቢሆንም፤ በአገልግሎቱ የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የሥራ ሞዴሉን ውጤታማነት በተግባር ማረጋገጡንም ጠቁመዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጀርመን አደባባይ አካባቢ ለህዝቡ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በዚሁ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች አገልግሎቱ ፈጣን እና ጊዜ ቆጣቢ መሆኑን ተናግረዋል። አቶ ኢብራሂም መሐመድ የመኪና ቦሎ ለማደስ ወደ ቦታው መሄዳቸውን ጠቁመው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ጨርሰው መመለሳቸውን ተናግረዋል። አቶ ብስራት ኮሬ እና አቶ ዘላለም አስረስም ለመንጃ ፈቃድና ለቦሎ ዕድሳት ወደ ተንቀሳቃሽ አውቶቡሱ በማቅናት፣ በአይነቱ ልዩና ቀልጣፋ መስተንግዶ ማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል። ያለምንም ስጋት ጊዜያቸውንም ቆጥበው በአገልግሎቱ ተጠቃሚ በመሆናቸው መደሰታቸውን ይናገራሉ። በተንቀሳቃሽ አገልግሎቱ ውስጥ የሚሰሩት የገቢዎች ባለሙያ ጫልቱ ታደሰ፣ ይህ አሰራር የተለመደውን በአንድ ቦታ ተወስኖ የመስራት አካሄድ በመቀየር ለተገልጋዩ ብቻ ሳይሆን ለአገልጋዩም ከፍተኛ የስራ ተነሳሽነትን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል። የንግድ ምዝገባ እና ፍቃድ ባለሙያ ብርሃኑ ፈንታው በበኩላቸው፣ ወደ ተገልጋዮች ቀርበው በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የመጀመሪያዎቹ ባለሙያዎች በመሆናቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ካባ መብራቱ፤ የመሶብ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ቀደም ሲል በሕዝብ ዘንድ ይነሳ የነበረውን ቅሬታ ለመፍታት መንግሥት የወሰደውን ቁርጠኛ አቋም የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። አዲሱ እሳቤ አገልግሎትን ከቢሮ በማውጣት ወደ ሕዝብ ይዞ የመጣ ድንቅ አሠራር መሆኑን አረጋግጠዋል።
የፀደቁ ደረጃዎች በዓለም አቀፍ ንግድ ተቀባይነትን መጨመር ያስችላሉ
Apr 24, 2026 97
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018(ኢዜአ)፦ በምግብ፣ በግብርና እንዲሁም በኮንስትራክሽንና ሲቪል ምህንድስና ዘርፎች የፀደቁ ደረጃዎች፣ በዓለም አቀፍ ንግድ ተቀባይነትን ከመጨመር ባለፈ የገቢ ምርቶች ጥራት ቁጥጥር ወጥ እና አስተማማኝ እንዲሆን እንደሚያስችሉ የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ገለፀ። ኢንስቲትዩቱ በምግብ፣ በግብርና እንዲሁም በኮንስትራክሽንና ሲቪል ምህንድስና ዘርፎች ላይ ያተኮሩ 66 ደረጃዎችን አጽድቋል፡፡ እነዚህ ደረጃዎች የሀገሪቱን ምርቶች በዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግና የገቢ ምርቶችን ጥራት ለመቆጣጠር ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸው ተገልጿል። ኢንስቲትዩቱ በምግብ ጨው ላይ የሚደረግ የደብል ፎርቲፊኬሽንን እንዲሁም ግንባታዎች ከንፋስና መሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የመከላከል አቅማቸውን የሚያሳድጉ ዘመናዊ የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ደረጃዎች በቦርድ መጽደቃቸውን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የኢንስቲትዩቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ሀብቴ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የደረጃዎች ቦርድ ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው 5ኛ መደበኛ ስብሰባው የቀረቡለትን 66 ደረጃዎች መርምሮ አጽድቋል፡፡ ካጸደቃቸው ደረጃዎች መካከል 24ቱ አዳዲስ ደረጃዎች ሲሆኑ 42ቱ የተከለሱ መሆናቸውን ጠቅሰው ከእነዚህም ውስጥ 54ቱ አስገዳጅ ደረጃዎች ሆነው መጽደቃቸው ጠቁመዋል፡፡ በምግብና ግብርና ዘርፍ የጸደቁት ደረጃዎች በተለይ በዜጎች ጤና ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመው በምግብ ጨው ላይ ፎሊክ አሲድ ተጨምሮ እንዲመረት የሚያስገድድ አዲስ ደረጃ መጽደቁንም ገልጸዋል፡፡ ይህም በእናቶችና በሕፃናት ላይ የሚስተዋሉ የጤና እክሎችን ለመቅረፍ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ከኮንስትራክሽን ጋር በተገናኘ የጸደቁት ደረጃዎች ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበትን የህንጻ ግንባታ እድገትና ዓለምአቀፍ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ያገናዘቡ ናቸውም ብለዋል። ግንባታዎች ከንፋስና ከመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች የተጠበቁ እንዲሆኑ የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ አጠቃቀሞች የተካተቱ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ የደብል ፎርቲፊኬሽንና ዘመናዊ የግንባታ ግብአቶችን በመጠቀም የግንባታዎችን የጥራት ደረጃ ማረጋገጥ የሚያስችሉ መመሪያዎች መቀመጣቸውንም ነው የጠቆሙት፡፡ ደረጃዎቹ መጽደቃቸው ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለምርምር፣ ለእውቀት ሽግግርና ለሸማቾች መብት መከበር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል። የሀገር ውስጥ ምርቶች በዓለም ገበያ ተቀባይነት እንዲኖራቸውና የገቢ ምርቶች ጥራት ወጥ በሆነ መንገድ እንዲፈተሹ የሚያስችል መሆኑንም አክለዋል፡፡ በተጨማሪም የዜጎችን ደህንነትና የአካባቢ ጥበቃን እንደሚያረጋግጥም አቶ ብሩክ ሀብቴ አስታውቀዋል፡፡ አምራቾችና አስመጪዎች የወጡትን ደረጃዎች አውቀው ምርቶቻቸውን በደረጃው መሠረት እንዲያቀርቡና ጥራታቸውን በማሻሻል ለዜጎች ደህንነትና ለሀገር ገጽታ ግንባታ የበኩላቸውን እንዲወጡ ኢንስቲትዩቱ ጥሪ አቅርቧል።
ስፖርት
ማንችስተር ሲቲ ለኤፍኤ ካፕ ፍጻሜ አለፈ
Apr 25, 2026 0
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኤፍኤ ካፕ የመጀመሪያ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ሳውዝሃምፕተንን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በዌምብሌይ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጄሬሚ ዶኩ እና ኒኮ ጎንዛሌዝ ለሲቲ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ፊናን አዛዝ ለሳውዝሃምፕተን ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ ለተከታታይ ዓመት ለኤፍኤ ካፕ ፍጻሜ አልፏል። ሲቲ በፍጻሜው ከቼልሲ እና ሊድስ ዩናይትድ አሸናፊ ጋር ይጫወታል። በሻምፒዮንሺፑ የሚገኘው ሳውዝሃምፕተን ከ23 ዓመታት በኋላ ለኤፍኤ ካፕ ፍጻሜ የማለፍ ህልማቸው አልተሳካም። የኤፍኤ ካፕ ሁለተኛ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በቼልሲ እና ሊድስ ዩናይትድ መካከል ነገ ይካሄዳል።
ባርሴሎና ጌታፌን በማሸነፍ ከሪያል ማድሪድ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 11 ከፍ አደረገ
Apr 25, 2026 108
አዲስ አበባ፤፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በስፔን ላሊጋ የ33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ባርሴሎና ጌታፌን 2 ለ 0 ረትቷል። ማምሻውን በኮሊሲየም ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፌርሚን ሎፔዝ እና ማርከስ ራሽፎርድ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ 28ኛ ድሉን ያስመዘገበው ባርሴሎና በ85 ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። ከተከታዩ ሪያል ማድሪድ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 11 ከፍ አድርጓል። ባርሴሎና የላሊጋውን ዋንጫ ለማንሳት ከቀሪ አምስት ጨዋታዎች የሚፈልገው ስድስት ነጥብ ብቻ ነው። በሊጉ 15ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ጌታፌ በ44 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሪያል ማድሪድ ትናንት ከሪያል ቤቲስ ጋር ባደረገው ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይቷል።
ሊቨርፑል ሲያሸንፍ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከድል ጋር ታርቋል
Apr 25, 2026 86
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 34ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መካሄዳቸውን እንደቀጠሉ ነው። በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሊቨርፑል ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 1 አሸንፏል። አሌክሳንደር ኢሳቅ፣ አንዲ ሮበርተስን እና ፍሎሪያን ዊትዝ ለሊቨርፑል ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ዳንኤል ሙኖዝ ለፓላስ ብቸኛውን ግብ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ሊቨርፑል በ58 ነጥብ ደረጃውን ከአምስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ በማድረግ የአስቶንቪላን ቦታ ተረክቧል። ሻምፒዮንስ ሊግ ለመግባት በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል። ክሪስታል ፓላስ በ43 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። በሞልኒው ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው መርሐ ግብር ቶተንሃም ሆትስፐርስ ዎልቭስን 1 ለ 0 አሸንፏል። ጆአኦ ፓሊንሃ በ82ኛው ደቂቃ ወሳኟን ግብ አስቆጥሯል። ከ15 ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ34 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ላለመውረድ በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። ከሊጉ መውረዱ የተረጋገጠው ዎልቭስ በ17 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ዌስትሃም ዩናይትድ በቶማስ ሱቼክ እና ካሉም ዊልሰን ጎሎች ኤቨርተንን 2 ለ 1 አሸንፏል። ኬርናን ዴውስበሪ-ሆል ለኤቨርተን ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ዌስትሃም ዩናይትድ በ36 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል። ከቶተንሃም ጋር ያለውን የሁለት ነጥብ ልዩነት በማስጠበቅ ላለመውረድ በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። ኤቨርተን በ47 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
የዋንጫ ተፎካካሪው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወሳኝ ድል ተቀዳጀ
Apr 25, 2026 88
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 22ኛ ሳምንት መርሀግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ አርባምንጭ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዳግማዊት ሰሎሞን እና ብርሃን ኃይለሥላሴ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ዳግማዊት ሰሎሞን (ኢትዮ ኤሌክትሪክ) የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። ኢትዮ ኤሌክትሪክ 18ኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን 57 ቢያደርስም፣ ተመሳሳይ ነጥብ ባለው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በግብ ክፍያ ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በሁለቱ ቡድኖች መካከል ያለው የዋንጫ ፉክክር አጓጊነቱ ጨምሯል። በውድድር ዓመቱ 16ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርባምንጭ ከተማ በ10 ነጥብ የመጨረሻውን 14ኛ ደረጃን ይዟል። አርባምንጭ ከተማ ባለፉት 15 የሊግ ጨዋታዎች ከድል ርቋል። በውድድር ዓመቱ ሁለት ጨዋታዎችን ብቻ ያሸነፈው ቡድኑ በሊጉ የመቆየት እድሉ ጠባብ ሆኗል። የኢትዮ ኤሌክትሪኳ አጥቂ ዳግማዊት ሰሎሞን በሊጉ ያስቆጠረቻቸውን ግቦች ወደ 23 ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቷን አጠናክራለች። ዛሬ በተደረገ ሌላኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ከተማን 3 ለ 0 በመርታት መሪነቱን አጠናክሯል።
አካባቢ ጥበቃ
ለአረንጓዴ አሻራ ልማት ስኬት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚና ላቀ ነው
Apr 24, 2026 105
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ለምግብ ዋስትና መሰረት ለሆነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስኬት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የላቀ ሚናቸውን ማስቀጠል እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ፡፡ የክልሉ ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ከክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ጋር በመተባበር በአረንጓዴ አሻራ ልማት ዙሪያ ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በሆሳዕና ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር እንደገለጹት፤ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ ትግበራ ከደን ልማቱ ባለፈ የስነ ምግብ ዋስትና መሰረት እየሆነ መጥቷል። በልማቱ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ያላቸውንና ለምግብ የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎችን በብዛትና በስፋት የማልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ለተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ለምግብ ዋስትና መሰረት ለሆነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስኬት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አንስተዋል። የስልጠናው ዓላማም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በእውቀትና መረጃ ላይ የተመሰረተ መረጃ ለህዝብ ተደራሽ ማድረግ እንዲችሉ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ዘሪሁን እሸቱ፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን በሚገባ ተገንዝበው የተሟላ መረጃ ለህዝብ ተደራሽ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። ለዚህም መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ወሳኝ እንደሆኑ አንስተው በቀጣይም በሙያቸው የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ በማስቀጠል ልማቱን እንዲያጠናክሩ አስገንዝበዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት፤ የኮሙኒኬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ ይኖራቸዋል
Apr 24, 2026 106
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረውን የአየር ሁኔታ ትንበያ አስመልክቶ ለኢዜአ መግለጫ ልኳል፡፡ በዚህም በሚቀጥሉት አስር ቀናት በርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚያገኙ አመላክቷል፡፡ በመግለጫው በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል፣ የስምጥ ሸለቆና አጎራባች አካባቢዎች፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እንዲሁም ሰሜን ምዕራብ እና ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተሻለ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚኖራቸው አስታውቋል፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች የሚኖረው ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ለቋሚ ተክሎች ዕድገት፣ ለግጦሽ ሳርና ለውሃ አቅርቦት መሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጿል። በሌላ በኩል ከዝናቡ ጋር ተያይዞ የመሬት መንሸራተት፣ የአፈር መሸርሸር እና ድንገተኛ ጎርፍ አደጋዎች ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ብሏል፡፡ በተጨማሪም በተደፋታማ ማሳዎች ላይ ውሃ መተኛት፣ የሰብል በሽታና ተባይ መከሰት እንዲሁም የአረም መስፋፋት ሊከሰት እንደሚችል ጠቅሷል፡፡ በዚህም በከተሞች በቆሻሻ የተደፈኑ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦዎችን ማጽዳትና የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎችን መሥራት ይገባል ብሏል በመግለጫው፡፡ የአፈርና ውሃ እቀባ ስራዎች እንዲሁም የእርከን ስራዎችን ማጠናከር፣ የሰብል በሽታና አረምን አስቀድሞ መከላከል እንዲሁም የእንስሳት መኖ መሰብሰብ እንደሚገባም አመላክቷል፡፡ በተጨማሪም ዝቅተኛ እርጥበት በሚገኝባቸው አካባቢዎች የዝናብ ውሃን በማሰባሰብና ደጋፊ መስኖን በመጠቀም የትነት መጠን የሚያስከትለውን ጉድለት መሙላት እንደሚገባ አስታውቋል፡፡ በአባይ፣ ባሮ አኮቦ፣ የላይኛው ኦሞ ጊቤ፣ ገናሌ ዳዋ እና ስምጥ ሸለቆ ተፋሰሶች ላይ ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ የገፀ-ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖርም በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ይህም ለኃይል ማመንጫ፣ ለመስኖና ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሻሻል ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁሞ፤ ህብረተሰቡ የጎርፍ አደጋን ለመከላከልና የሚገኘውን እርጥበት በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባውም አሳስቧል፡፡
በብሔረሰብ አሥተዳደሩ ሥነ-ምኅዳርን መሠረት ያደረጉ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው
Apr 24, 2026 97
ሰቆጣ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በመጪው ክረምት ሥነ-ምኅዳርን መሠረት ያደረጉ ችግኞችን ለመትከል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የዋግኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የደን ባለሙያ ታደሠ መሳይ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ አሥተዳደሩ ዝናብ አጠር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የተፈጥሮ ሃብት ሥራና የደን ልማት ተግባራት በከፍተኛ ትጋት እየተሠራበት ነው። በዚህም እስካሁን 3 ነጥብ 7 ሚሊየን ችግኞችን ለተከላ ዝግጁ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው፤ ችግኞቹ ምኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውና ሀገር በቀል ናቸው ብለዋል። በበጋው ወራት የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ የተሠራበትን ጨምሮ ከ2 ሺህ 130 ሔክታር በላይ መሬት በመለየት የችግኝ መትከያ ጉድጓድ የማስቆፈር ሥራ እየተሠራ መሆኑንም አስረድተዋል። ባለፉት ዓመታት ሥነ-ምኅዳሩንና የአየር ንብረቱን መሠረት ያደረጉ ችግኞችን በመትከል አካባቢውን ወደ ምርታማነት የመለወጥ ሥራ ውጤት በማሳየቱ፤ ሕብረተሰቡ ለተፈጥሮ ሃብት ሥራ ከፍተኛ ፍላጎት ማሳየቱን ጠቁመዋል።
በምሥራቅ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ ነው
Apr 23, 2026 110
ነቀምቴ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦በምሥራቅ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት የሚተከሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። በጽሕፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ በለጠ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ ነው። በዘንድሮው መርሐ ግብር ለሁሉም የችግኝ ዓይነቶች ትኩረት ቢሰጥም፣ ይበልጥ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ዝርያዎች ላይ ትኩረት ተደርጓል ነው ያሉት። እየፈሉ ከሚገኙት ችግኞች መካከል አትክልትና ፍራፍሬ፣ የደንና ጥምር ደን ዝርያዎች፣ ቀርከሃ፣ የእንስሳት መኖ የሚገኙበት መሆኑን ነው የተናገሩት። የእጽዋት ስብጥሩ ከአካባቢው አየር ንብረት ጋር የሚስማማና በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤት የሚሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ካለፉት ዓመታት ተሞክሮ በመነሳት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የጉድጓድ ዝግጅት መጀመሩን የጠቆሙት አቶ ደሳለኝ፤ የአየር ንብረት ጥናት፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ እንዲሁም የሕብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያሳድጉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። ለዘንድሮው ተከላ የሚውል 107 ሺህ ሄክታር መሬት የተዘጋጀ ሲሆን፣ በዞኑ በሚገኙ 2 ሺህ 194 የመንግሥትና የግል የችግኝ ጣቢያዎችም የችግኝ እንክብካቤ ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው ችግኝ መትከል ከመደበኛ መርሐ ግብር ባለፈ የሥራ ባሕላቸው እየሆነ መምጣቱን ይናገራሉ። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ወይዘሮ አዲስዓለም በለጠ ባለፉት ዓመታት በተተከሉ ችግኞች በአካባቢው የተፈጥሮ ሀብት ለውጥ መታየቱን ገልጸዋል። አቶ ተሰማ መኮንንም በተመሳሳይ ቀደም ሲል ለደን የነበረው ዝቅተኛ አመለካከት ተቀይሮ፣ ዛሬ ሕብረተሰቡ የተራቆቱ ቦታዎችን መልሶ በማልማትና በመንከባከብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለዘንድሮው ተከላም አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 491
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 395
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 683
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት። ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው
Mar 22, 2026 374
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሐተታዎች
ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር
Apr 23, 2026 228
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት በቢሾፍቱ ከተማ በይፋ መጀመሯን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል። ጋዜጠኛ ዳንኤል ኦሊቫሬስ ጋሌጎ በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ እንደገለጸው፣ ይህ ሜጋ ፕሮጀክት አፍሪካውያን ተጓዦች ከአህጉሩ ውጭ ባሉ እንደ ዱባይ፣ ፓሪስና ለንደን ባሉ ማዕከላት በኩል የሚያደርጉትን አድካሚ ጉዞ በማስቀረት፣ አዲስ አበባን የአህጉሪቱ ቀዳሚ የመገናኛ ማዕከል ለማድረግ ያለመ ነው። ከአዲስ አበባ ከተማ በስተደቡብ ምስራቅ 48 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ይህ ግዙፍ ግንባታ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ተብሎ መጠቀሱን ጋዜጠኛው በዚሁ ጽሁፉ አመልክቷል። ስራው በይፋ የተጀመረው ባለፈው ጥር ወር ሲሆን፣ አውሮፕላን ማረፊያው በ2023 ዓ.ም (2030 እ.ኤ.አ) የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር፣ በዓመት 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም እንደሚኖረው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ተመልክቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ፣ ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል። ይህም አውሮፕላን ማረፊያውን በዓለም ላይ በርካታ ተጓዦችን ከሚያስተናግደው የአትላንታው ሀርትስፊልድ-ጃክሰን አውሮፕላን ማረፊያ ካለው አቅም በላይ እንደሚያደርገው ዳንኤል ኦሊቫሬስ ጋሌጎ ባሰፈረው ጽሁፍ አብራርቷል። አውሮፕላን ማረፊያው ከመንገደኞች አገልግሎት ባለፈ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠናን (AfCFTA) በላቀ ሁኔታ ለመደገፍ ታቅዶ የተገነባ መሆኑን ጋዜጠኛው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ በዝርዝር አስቀምጧል። በዓመት 3 ነጥብ 73 ሚሊዮን ቶን ጭነት የማስተናገድ አቅም ያለው ይህ መሠረተ ልማት፣ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የአፍሪካን የጭነት በረራ ፍላጎት በሚገባ ምላሽ መስጠት የሚችል መሆኑን ተጠቁሟል። የአውሮፕላን ማረፊያው የተርሚናል ዲዛይን በዓለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ በሆነው ዛሃ ሃዲድ አርክቴክትስ የቀረበ መሆኑን የጠቀሰው ጋዜጠኛው፣ዲዛይኑ የኢትዮጵያን ታላቁ ስምጥ ሸለቆና የተለያየ መልክዓ ምድራዊ ውበትን የሚያንፀባርቅ መሆኑን በጽሁፉ አካቷል። ተጓዦች በአውሮፕላን ማረፊያው ውስጥ ሲዘዋወሩ የኢትዮጵያን ባህልና ተፈጥሮ እንዲመለከቱ በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን፣ለዘላቂነት ቅድሚያ በመስጠት የፀሐይ ብርሃን ኃይልንና የዝናብ ውሃ አሰባሰብ ስርዓትን እንዲጠቀም ተደርጎ ተቀርጿል። በአጠቃላይ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጠናቀቅ፣ኢትዮጵያ በአፍሪካ አቪዬሽን ያላትን መሪነት ከማረጋገጡ ባለፈ የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ትስስር ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ጋዜጠኛው በሲኤንኤን የጉዞ ገጽ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ደምድሟል። ይህ ፕሮጀክት ከሌሎች የአፍሪካ አየር መንገዶች ጋር በመተባበር የነጠላ የአፍሪካ አየር ትራንስፖርት ገበያን (SAATM) ወደ ተግባር ለመቀየር የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እንደሚያግዝም ተመልክቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 19, 2026 329
የምግብ ሉዓላዊነት - ከተረጂነት መላቀቂያው መንገድ በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ ከተረጂነትና ጠባቂነት መፋቻ መንገዶች መካከል የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አንዱ ብልኀት አድርጋ እየታተረች ነው። ይህን ተከትሎም የዜጎችን የምግብ ፍላጎት በራስ የምርት ዐቅም የመሸፈን ሥራ በመከወን ከጠባቂነት ለመላቀቅ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ስኬታማ ናቸው። ለዚህም ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ከልመና ወጥታ ወደ ውጭ ገበያ መላክ መጀመሯ አሥረጅ ነው። በመሆኑም ከውጭ የኢኮኖሚ ጥገኝነት በመላቀቅ የዜጎችን የምግብ ሉዓላዊነት ለማስከበር በስንዴ ልማት የተመዘገበውን ስኬት በሌሎች የግብርና ዘርፎች ለመድገም ርብርብ እየተደረገ ነው። በዚህም መሠረት በሩዝ፣ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ሻይ ቅጠል እና ሌሎች የተለያዩ ሰብሎች ላይ እየተከናወነ ያለው ሥራ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው። የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የግብርና ድርጅት (ፋኦ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምግብ ዋስትናና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ የአመራር ቁርጠኝነት የአግሪኮላ ሜዳሊያ በ2016 ዓ.ም ማበርከቱ ለምግብ ሉዓላዊነት ጥረት የተሰጠ ዕውቅና ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ረሃብን ከማስቀረት ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ብሔራዊ ብልጽግናን ዕውን ለማድረግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሃብቶች፣ተስማሚ የዓየር ንብረት፣ ለሥራ ትጉ የሆነ ወጣት እንዳላት እና እነዚህን ሃብቶች ታሳቢ በማድረግ የታሪክ ዐውራ የሆነችውን ሀገር ልማት ወደፊት ለማራመድ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል። በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ እንደከፈልን ሁሉ፤ ከምግብ ጥገኝነት ለመላቀቅ በትጋት መሥራት ይገባል ሲሉ ማስገንዘባቸው ይታወሳል። የምግብ ሉዓላዊነት፣የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት፣ የበጀት ሉዓላዊነት ታላቁን የሀገር ሉዓላዊነት በጽናት የሚያቆሙ መሆናቸውንም አብራርተዋል። እነዚህን የሉዓላዊነት ዘርፎች ለማስከበርም ብሔራዊ ዐርበኝነት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። ሀገራዊ ትልሙ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት የሚያሸጋግር መልካም ጅማሮ ነው።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 19, 2026 164
ክልሎች፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የንፋስ ሃይል በቀጥታ የምናመራው በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ኢተያ አካባቢ ነው። በኢተያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው የመረቁትን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን እንመለከታለን። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 100 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ሲሆን ኢትዮጵያ በታዳሽ ሃይል ልማት ወደ ፊት እየተራመደች መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ሥራ ነው። ኢትዮጵያ ዘንድሮ ከጉባ እስከ አሰላ፣ ገናሌ እና አይሻ በሃይል ልማት ዘርፍ ትልቅ ትርጉም ያላቸውን ፕሮጀክቶች አስመርቃለች። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ደግሞ በዚህ ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀምሯል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በምርቃቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ከለውጡ በፊት የነበረው 4 ሺህ ሜጋ ዋት የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅም አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት በመድረስ ከእጥፍ በላይ እድገት የተመዘገበበትን ትልቅ ስኬት አንስተዋል። የስንዴና ገብስ ሰብሎችን በከፍተኛ መጠን የሚያመርተው አርሲና አካባቢው አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ሃይል የሚመረትበት አካባቢ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ እናስቀጥላለን ሲሉ አረጋግጠዋል። ቢሾፍቱ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማም በዚህ ሳምንት በቢሾፍቱ ሀርሰዴ አዳራሽ መካሄዱ ይታወቃል። በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ስኬታማ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። በተለይም የክልሉን ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተሻለ መልኩ ያሳደጉ የከተማ እና የገጠር የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ነው ያስረዱት። ከዚህ ባለፈ የክልሉን የልማት ሥራዎች ለማቀላጠፍ የሚያግዙ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የአገልግሎት አሰጣጥ አሰራሮች መተግበራቸውንም ተናግረዋል። የቢሾፍቱ መድረክ በድምሩ የግብርና፣ የገጠርና የከተሞች ልማት፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ክንውን በዝርዝር የታየበት ውጤታማ መድረክ እንደነበረም ተመላክቷል። የአሎማ ክላስተር ሌላ የሳምንቱ ዓበይት ጉዳይ ወደ አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ይወስደናል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በይፋ አገልግሎት መስጠት የጀመረው በዚህ ሳምንት ነው። በመስኖ የለማ የስንዴ ክላስተር የተጎበኘበትና በተሁለደሬ ወረዳ በክላስተር ለሚከናወነው የተቀናጀ የፍራፍሬ ልማት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ የተጀመረበት እንዲሁም የክልሉ የ10 ዓመት የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ ይፋ የተደረገበትን ሁነት እናገኛለን። በእነዚህ ሁነቶች ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የመደመር መንግሥት በሁሉም ዘርፎች ለሀገር እድገትና ማንሰራራት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም በግብርና፣ በመስኖ ልማት፣ በቱሪዝምና ሌሎች መስኮች በተግባር የተመለከትናቸው የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ማሳያዎች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። የአሎማ ክላስተር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የሓይቅ ዳር አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የማቻል ጥረት በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን የሚያሳዩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሀገርን የማሻገር ሥራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የታሪክ መሰነጃ የሳምንቱ በረራችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ የሰው ልጅ መገኛ፣ የኤርታሌ ትኩሳት የሚገነፍልባትና የአዋሽ ወንዝ የተንጣለለባት አፋር ክልል ገብተናል። በአፋር ቆይታችን ትኩረታችንን ሰመራ በማድረግ በስፍራው ሊገነባ የታሰበውን የሉሲ ሙዚየም እንመለከታለን። ሙዚየሙን ለመገንባት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እና የአፋር ክልል ቱሪዝም ቢሮ የፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት አድርገዋል። ለሉሲ አፋር ቤቷ ነው፤ ሀዳር የተባለው ስፍራ ደግሞ መገኛዋ ነው። በመሆኑም በዚህ ከሰው ልጅ መገኛ ጋር የተቆራኘን ስፍራ ሙዚየም ገንብቶ፣ የቱሪስት መስህብ አልምቶና አካባቢውን በስፋት አስተዋውቆ የገቢ ምንጭ ማድረግ ሲቻል ለምን ተዘንግቶ ቆየ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ይሆናል። የጊዜ ጉዳይ ሆኖ አሁን አፋር ሰመራ ላይ በሉሲ የተሰየመ የሀገር ታሪክና ቅርስ ማጣቀሻ፤ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ማሳያ የሆነ ሙዚየም ለመገንባት ዝግጅት መደረጉ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር)፤ የሚገነባው ሙዚየም የሀገር ታሪክና ቅርስ የሚሰነድበት፣ የአፋር ክልል ህዝብ ቱባ ባህሎች ተጠብቀው የሚዘልቁበት፣ የሰው ልጅ አመጣጥና ዝግመተ ለውጥ የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ የሚካሄድበት ይሆናል ብለዋል። እሳቸው እንዳሉት የሙዚየሙ ግንባታ በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገለግሎት የሚበቃ ይሆናል። የአፋር ክልል በመስኖ ቢያለሙበት፣ የጥጥ እና የቴምር ልማት ቢካሄድበት ተዝቆ የማያልቅ እምቅ አቅም ያለው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በለውጡ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን እምቅ የቱሪዝም ሃብቱንም በማልማትና በመጠበቅ የሃገር ሃብት የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የሉሲ ሙዚየም ግንባታ ሁነኛ ማሳያ ነው። የሳምንቱ ቅኝታችን እንደቀጠለ ሲሆን አሁን ደግሞ በቀጥታ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ አሶሳ ተገኝተናል። አሶሳ በሳምንቱ በሃይማኖት አባቶች ጸሎትና ዱአ ተባርካ ስለ ሰላምና አብሮነት የሚመከርባት ከተማ ሆና እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። የተለያዩ የኃይማኖት አባቶች፣ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት 7ኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ "ሰላምን ይበልጥ ለማስፋት እና ለማስረጽ የሃይማኖቶች ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ አባቶች ስለ ሰላም እና አብሮነት እንትጋ ለትውልድ ግንባታም መስራት ግድ ይለናል በማለት አፅንኦት በመስጠት መክረዋል። የኢትዮጵያ ሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ኃይማኖቶች ለሰላም እና ለህዝቦች አብሮነት ያላቸውን አስተምህሮ በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም ግንባታ እና ሀገራዊ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆን አለባቸው ብለዋል። በኢትዮጵያ ሰላምን ለማጽናት እና የወንድማማችነት ድልድይን ለመገንባት እንስራ በማለትም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ከአሶሳ ወደ ሀዋሳ ስንጓዝ የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ-AGRA) ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች የኤልቶ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ዩኒየን የሥራ እንቅስቃሴን መጎብኘታቸውን እናገኛለን። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጥምረቱ የቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ አርሶ አደሮች ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ጥሩ ተስፋ የተሰነቀበት መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል። የግብርና ልማትን የማዘመን፣ ምርታማነትን የማሳደግና የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር መሆኑንም አፅንኦት ሰጥተዋል። የጥምረቱ ፕሬዚዳንት አሊስ ሩህዌዛ፤ በአፍሪካ የግብርና ስርዓት ሽግግርን ለማጠናከር በተለይም አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል። በአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ሂደት ውስጥ ደግሞ የኢትዮጵያ ለውጥ አስደናቂ ስለመሆኑ አንስተዋል። ሌሎች በዚህ ሳምንት በሁሉም ክልሎች ባደረግነው ምልክታ በተለይም የምርጫ ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳ ሆኖ ዜጎች የምርጫ ካርዳቸውን እየወሰዱ ሲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎችም የምረጡኝ ቅስቃሳ ማድርጋቸውን ቀጥለዋል። የግብርና ልማት ስራዎች፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ዝግጅት እና ሌሎችም የልማት ሥራዎች በተጠናከረ መልኩ የቀጠሉበት ሳምንት ነበር ማለት ይቻላል።
የጤና ነገር …
Apr 17, 2026 367
በዮሐንስ ደርበው ማዲያት ታክሞ ይድናል? እነማንንስ ያጠቃል? የሥነ-ውበት ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ሱመያ ኑርሁሴን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለማዲያት መንስዔ፣ ምልክቶች እና ሕክምና ሙያዊ ሐሳባቸውን አጋርተዋል። እንደ ባለሙያ ቢደረግ ያሉትንም መክረዋል። • ማዲያት እነማንን ያጠቃል? ማዲያት ማንኛውንም ሰው እንደሚያጠቃ ያነሱት ዶ/ር ሱመያ፤ በብዛት ግን በሴቶች ላይ እንደሚከሰት ያስረዳሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ እርግዝና ላይ ያሉ እንዲሁም የወሊድ መከላከያ የሚወስዱ ሴቶች እና ሆርሞናል ቴራፒ ላይ ያሉ ሰዎች በስፋት ለማዲያት ተጋላጭ ናቸው። በተጨማሪም በብዛት ምግብ ማብሰል (ኪችን) ላይ የሚሠሩ ሰዎች ለማዲያት እንደሚጋለጡ ጠቁመዋል። ባብዛኛው ማዲያት የሚያጠቃው በዕድሜ ከ25 ወይም ከ30ዎቹ በላይ የሆኑትን መሆኑንም አንስተዋል። • መንስዔ እንደ ዶክተር ሱመያ ገለጻ፤ ለማዲያት ከሚያጋልጡ መንስዔዎች መካከል ዋነኛው የፀሐይ ጨረር ነው። በተጨማሪም ሆርሞናል ፋክተር (የወሊድ መከላከያ መጠቀም፣ እርግዝና ላይ መሆን፣ ሆርሞናል ቴራፒ መውሰድ) ለማዲያት አጋላጭ መንስዔ ሆነው ይጠቀሳሉ ይላሉ። ጭንቀት እንዲሁም ቆዳን የሚያስቆጡ ነገሮች ለማዲያት አጋላጭ መሆናቸውንም ነው ያብራሩት። • ምልክቶች ማዲያት ቀላ፣ ጠቆር ወይም ደብዘዝ ያለ ቀለም (መልክ) ይዞ ከትንሽ ጀምሮ የሚሰፋ መሆኑን ዶክተር ሱመያ አስገንዝበዋል። ለምሳሌ ይላሉ፤ ጉንጭ ላይ መውጣት ቢጀምር ወደ ሁለቱም ጉንጮች ከዚያም ወደ ግንባር እንዲሁም አገጭ እና አፍንጫ ሊደርስ እንደሚችል ገልጸዋል። በሂደትም የማቃጠል፣ የመቆጥቆጥ እና ማሳከክ ሁኔታ ሊኖረው እንደሚችል ነው ያነሱት። • ሕክምና መንስዔዎቹን ዐውቆ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ያስገነዘቡት ዶክተር ሱመያ፤ የፀሐይ ጨረር መከላከያዎችን መጠቀም፣ በሕክምና የሚሰጡ መድኃኒቶችን ሳያቋርጡ በትዕግስት መጨረስ (ቶሎ ለውጥ አላየሁበትም ብሎ አለማቋረጥ) እንደሚገባም መክረዋል። የማዲያት ሕክምና ስኬታማነቱ ለሁሉም ሰው በዕኩል ጊዜ እንደማይታይ በመግለጽ፤ እንደተከሰተበት ጊዜ ከሰው ሰው እንደሚለያይ በአጽኦት ተናግረዋል። ለምሳሌ አሉ፤ ዓመታት ያለፉት ማዲያት እና 2 ወራት የሆኑት ሕክምና እኩል ቢጀመርም በተመሳሳይ ጊዜ ላይድኑ እንደሚችሉ አመላክተዋል። ስለዚህ የሌላኛው ድኖ የኔ አልዳነም በሚል ሕክምናን ማቋረጥ ስህተት መሆኑንም ነው ያስረዱት። በሌላ በኩል ማዲያትን አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አረጋግጠው፤ ይህም የሚሆነው መንስዔዎቹን በማወቅ የማዲያት ተጋላጭ ባለመሆን ነው ብለዋል። ከተቻለ በየሥድስት ወሩ ወይም በየዓመቱ የቆዳ ጤና ምርመራ ማድረግ እና ያለበትን ደረጃ ማወቅም የሚከሰት ችግር ቢኖር እንኳ ሥር ሳይሰድድ በማከም ቶሎ እንዲድን ማድረግ ይቻላል ነው ያሉት።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 102
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ጤና ከሀገር በቀል ስኬት ወደ አህጉራዊ መሪነት
Apr 23, 2026 195
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ እያከናወነች ያለችው ስራ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂካዊ የሆኑ ተቋማዊና የፖሊሲ መሰረቶች ተጥለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መቋቋም ለሀገራዊ ችግሮች በቴክኖሎጂ የታገዘ መፍትሄ ለማግኘት ትልቅ አቅም የፈጠረ ሲሆን፣ ብሄራዊ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፖሊሲ ተቀርጾ መጽደቁ ደግሞ የዘርፉን ልማትና አጠቃቀም በተደራጀ መንገድ ለመምራት አስችሏል። እነዚህ እርምጃዎች ሀገሪቱ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እና 2030 ስትራቴጂ ውስጥ ቴክኖሎጂውን እንደ ቁልፍ የለውጥ አቅጣጫ እንድትጠቀም በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የቴክኖሎጂ ሽግግሩን ዘላቂ ለማድረግም በሰው ኃይል ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። በአሁኑ ወቅት አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በኮዲንግ፣ በዳታ ሳይንስ እና በክህሎት ለማሰልጠን የተጀመረው ግዙፍ ፕሮግራም የለውጡ አንቀሳቃሽ ኃይል እየሆነ ነው። ከዚህም ባለፈ፣ በአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ እንዲገነባ መታቀዱና በዚህ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባልነት ውስጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት እንዲሳተፍ መወሰኑ፣ ሀገሪቱ ቴክኖሎጂውን ለውሳኔ ጥራትና ለምርምር በከፍተኛ ደረጃ እየተጠቀመችበት መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ እንደገለጸው፣ ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በሹመት ደብዳቤው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ AI ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ ማድረጉ ተመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አክሎ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የAI አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል እና በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ለሀገራዊ ለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ በዝርዝር አስፍሯል። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የAI ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የተያዘው ሥራ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክርም ተገልጿል። ይህ አህጉራዊ እውቅና በተለይ በጤናው ዘርፍ የታዩ ውጤቶችን ያካትታል። ኢትዮጵያ በኤአይ የታገዘ ዲጂታል ኤክስሬይን ለሳንባ ነቀርሳ ምርመራ ካዋሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። በተጨማሪም የ"HEP Assist" መተግበሪያን በሙከራ ደረጃ በማስጀመር፣ በገጠር የሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ውስብስብ ምልክቶችን ሲያዩ ሙያዊ የሕክምና ውሳኔ እንዲሰጡ ድጋፍ እየተደረገ ነው። እነዚህ የዲጂታል ጤና ስራዎች በ7 ክልሎችና በ15 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ መጀመራቸው፣ ቴክኖሎጂው በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የአገልግሎት ልዩነት ለማጥበብ ያለውን ፋይዳ ያሳያል። በአጠቃላይ፣ የኤአይ ቴክኖሎጂ በጤናው ዘርፍ ከሚሰጠው የጡት ካንሰር፣ የአንጎል እብጠትና የቆዳ በሽታዎች ምርመራ ባለፈ፣ በግብርና፣ በፋይናንስና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥም በስፋት እየገባ ይገኛል። በ2030 በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ሆስፒታሎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል አገልግሎት ለመቀየር የተቀመጠው ግብ፣ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የጀመረችውን የቴክኖሎጂ ነጻነትና የመሪነት ጉዞ ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓት በጤና፣ በግብርና እና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በጤናው ዘርፍ እንደ ካንሰር እና ሳንባ ነቀርሳ ያሉ በሽታዎችን ቀድሞ በመለየት የህክምና ጥራትን ሲያሻሽል፣ በግብርናው ደግሞ የሰብል ተባዮችንና የቡና በሽታዎችን በመለየት ምርታማነትን እያሳደገ ነው። ከዚህ ባለፈም ቴክኖሎጂው በመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥ እና በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ሰፊ የመረጃ ትንታኔዎችን በፍጥነት በማከናወን፣ የሥራ ፍጥነትን እና የውሳኔ አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ ይገኛል። የዘርፉ ፋይዳ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባለፈ የሀገሪቱን የዲጂታል ሉዓላዊነት እና የሰው ኃይል አቅም በመገንባት ላይ ያተኩራል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶችን በኮዲንግ እና በዳታ ሳይንስ በማሰልጠን እንዲሁም የፈጠራ ማዕከላትን (Startups) በመገንባት፣ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በሌሎች ላይ ጥገኛ ከመሆን ወጥታ የራሷን የዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ይህም በአህጉር ደረጃ ለሚደረጉ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች እንደ አርአያ በመሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ ፍትሃዊነት የመጠቀም ጥቅል ፋይዳው የጎላ እንዲሆን አድርጎታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሹመት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ ያጎላል። በተጨማሪም ሹመቱ የኢትዮጵያ ተሞክሮ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ማግኘቱንና አፍሪካ በኃላፊነትና በፍትሐዊነት በታጀበ የኤአይ አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንድትሆን የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣም ያደርጋታል።
ኢትዮጵያ በአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ መንገድ
Apr 21, 2026 1443
(በዮሐንስ ደርበው) ታሪክ እንደሚነግረን፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥቅም ለመጀመሪያ ጊዜ ዕውቅና ያገኘው የኢንዱስትሪያዊ ንብረት ጥበቃን በሚመለከተው በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1883 በተፈረመው የፓሪስ ስምምነት እንዲሁም፤ በ1886 የተፈረመውን የሥነ-ጽሑፍና ሥነ-ጥበብ ሥራዎች ጥበቃን የተመለከተውን የበርን(ስዊዘርላንድ) ስምምነት ተከትሎ ነው። እነዚህ ስምምነቶችም በዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት የሚተዳደሩ መሆናቸው ይታወቃል። ኢትዮጵያ የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣንን፤ በ2022 ዓ.ም ፈጠራንና ኢኖቬሽንን በማበረታታት የፈጠራ ሐሳቦችን ወደ ዕሴት በመለወጥ ሂደት ለሀገራዊ ብልጽግና ቁልፍ ሚና የሚጫወት በአፍሪካ ተምሳሌት የአዕምሯዊ ንብረት ተቋም ለማድረግ እየታተረች ነው። ለዚህ ርዕይ መሳካትም፤ ተቋሙ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት ለሀገራዊ ፈጠራ መጎልበት፣ የኢኖቬሽን፣ ቴክኖሊጂ ሽግግር እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ማደግ ጥቅም ላይ የሚውልበትን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ሀገራዊ የመዋቅር ሽግግርን መደገፍ የሚል ተልዕኮ አንግቦ እየሠራ ይገኛል። የእስካሁኑ የንግድ ምልክት፣ ቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና የፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) ምዝገባ የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ወርቅነህ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ2015 ዓ.ም እስከ ያዝነው በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ድረስ በንግድ ምልክት፣ በቅጅና ተዛማጅ መብቶች እና በፈጠራ ባለቤትነት (ፓተንት) 20 ሺህ 476 ምዝገባዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። በዚህም መሠረት ይላሉ፤ 14 ሺህ 729 የንግድ ምልክቶች፣ 5 ሺህ 254 የቅጅና ተዛማጅ መብቶች እንዲሁም 1 ሺህ 781 የፈጠራ ሥራ ባለቤትነት ምዝገባ በተቋማችን አማካኝነት ተከናውኗል። የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች ምንድን ናቸው? አዕምሯዊ ንብረት ማለት በሰው ልጅ አዕምሮ የሚፈጠሩ የፈጠራ ሥራዎችን የሚመለከት መሆኑን የገለፁት አቶ ብሩክ፤ እነዚህ የፈጠራ ሥራዎች እንደማንኛውም ቁሳዊ ሀብት በንብረትነት የሚታወቁበትን አግባብ የያዘው ሥርዓት ደግሞ የአዕምሯዊ ንብረት መብት እንደሚሰኝ ያስረዳሉ። በዚህ አግባብ፤ የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች እንደማንኛውም ቁሳዊ ንብረት ሁሉ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ባለመብቶች የሚሰጡ የባለቤትነት መብቶች መሆናቸውን እንረዳለን። ለዚህም እንደ ምክንያት የሚቀርበው እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፤ ወጥ ሥራዎችን ለማመንጨት የፈጠራ ባለመብቶች ዕውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውንና ጊዜያቸውን መስዋዕት በማድረግ ከብዙ ድካም በኋላ ያገኟቸው የፈጠራ ውጤቶች በመሆናቸው ነው። ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ ለምን አስፈለገ? አንድም፤ የሰው ልጅ ቀጣይ ዕድገትና የኑሮ ደኅንነት ዋስትና መሠረት የሚያርፈው በቴክኖሎጂና ባሕል ዘርፎች በሚያሳርፋቸው ፈጠራዊ ብቃቶቹ በመሆኑ እንዲሁም የምርምርና የፈጠራ ሥራዎችን ለማካሄድ ተጨማሪ ሀብት የሚያስገኝ በመሆኑና ይህም የኢኖቬሽን ሥርዓቱን ስለሚያሳድግ ነው ይላሉ አቶ ብሩክ። እንዲሁም፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃና ዘርፉን ለሕዝብ የማስተዋወቅ ተግባር ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን በማረጋገጥ የድርሻውን ስለሚወጣና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት በአጠቃላይ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ በተሻለ ደረጃ ላይ እንዲቆም ስለሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም፤ ሀገራት ጠንካራ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠሩ ቁጥር ዘርፉ ለኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ የልማት መሣሪያ መሆኑን ይገነዘባሉ። ጠንካራና ፍትሐዊ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት በፈጠራ ባለቤቶችና በተጠቃሚው ሕዝብ ዘንድ ሚዛናዊ ነው ያሉት አቶ ብሩክ። በአጠቃላይ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ለአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ማድረግ በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን በአጽነዖት አንስተዋል። ዜጎች በአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት እንዴት ተጠቃሚ ይሆናሉ? ባለብዙ ቢሊየን ዶላር የፊልምና ድምጽ ሪከርድስ አሳታሚዎችና ሶፍትዌር ኢንዱስትሪዎች ለብዙ ሚሊየኖች የመዝናኛ ሥራዎች የሚያበረክቱት የቅጅ መብት ጥበቃ በመኖሩ መሆኑን መገንዘብ እንደሚገባም አቶ ብሩክ ይናገራሉ። በሌላ በኩል ተጠቃሚዎች የሚፈልጓቸውን ምርቶችና አገልግሎቶችን መለየት የሚያስችላቸው ብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ የንግድ ምልክቶች ጥበቃና የመብት ማስከበር ሥርዓቶች ባይኖሩ ኖሮ ተመሳስለው በሚቀርቡ ምርቶችና አገልግሎቶች መታለልና ሌሎችም ችግሮች ያጋጥማቸው እንደነበርም ጠቁመዋል። ስለዚህ ምርቶችን በመሸመት ሂደትም በምርቶችና አገልግሎቶች ላይ ያለምንም ግራ መጋባት ግብይቱን ማከናወን እንደሚያስችላቸው መገንዘብ ይቻላል። እንደ አቶ ብሩክ ገለጻ፤ ለፓተንት የፈጠራ ሥራዎች ጥበቃ በመደረጉ መሰጠት የሚገባቸው ማበረታቻዎች የማይሰጡ ከሆነ፤ የፈጠራ ባለሙያዎች ቀጣይ የምርምር ሥራዎችን ማሳደግና ማስፋት እንደማይችሉ ይገመታል። በቀጣይነት የሚገኙ የተሻሻሉ የፈጠራ ሥራዎች አለመኖራቸው ደግሞ፤ በምርቶች ተጠቃሚና አጠቃላይ የኑሮ መሻሻል ሂደት ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተፅዕኖ ይኖረዋል። የአዕምሯዊ ንብረት ዓይነቶች እንዴት ይመደባሉ? የአዕምሯዊ ንብረት፤ የኢንዱስትሪያዊ ንብረት (Industrial Property) እና የቅጅና ተዛማጅ መብቶች (Copyright and Related Rights) በሚሉ ሁለት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚመደብ ያስረዳሉ። አክለውም፤ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት በውስጡ፤ የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ የኢንዱስትሪያዊ ንድፍ እና የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች የተሰኙ አራት ክፍሎችን እንደሚይዝ ያብራራሉ። ፓተንት ምንድን ነው?፡- ፓተንት ማለት በአንድ ቴክኒካዊ ባሕርይ ባለው የፈጠራ ሥራ ላይ የሚኖር የፈጠራ ባለቤትነት ብቸኛ መብት መሆኑን አቶ ብሩክ አስረድተዋል። የፓተንት መብት በአንድ ምርት (ለምሳሌ ማሽን ወይም የአመራረት ሂደት (Process) ሊሰጥ የሚችል ሲሆን፤ ፈጠራውም ለአንድ ቴክኒካዊ ችግር መፍትሔ የሚያስገኝ መሆን ይኖርበታል ይላሉ። ከፈጠራ ሥራው አመንጪ ይሁንታ ውጭ ሥራውን ገበያ ላይ ማዋል፣ መጠቀም፣ ማሰራጨት፣ መሸጥ ወዘተ… እንደማይቻልም አክለዋል። ፓተንት ለባለ መብቱ የጥበቃ መብት የሚያስገኝ ሲሆን፤ የጥበቃው ዘመንም በአጠቃላይ እስከ 20 ዓመት ሊደርስ ይችላል። ፓተንት የሚያስገኛቸው ሕጋዊ (የጥበቃ) መብቶች፡- የፈጠራ ሥራውን መጠቀም የሚችሉና የማይችሉ ሰዎችን መወሰን፤ ሦስተኛ ወገኖች ሥራውን እንዲጠቀሙ የመፍቀድ ወይም የፈቃድ ውል ስምምነት የመስጠት እንዲሁም የፈጠራ ሥራውን የመሸጥ (ለአዲስ የፓተንት ባለመብት) የሚሉት ይገኙበታል ብለዋል ሥራ አስፈጻሚው። የፓተንት ሥራዎች ለምን ያስፈልጋሉ?፡- ይህን ሲያብራሩም፤ ፓተንት ለፈጠራ ባለመብቶች ዕውቅናንና ሽልማቶችን (ማበረታቻዎችን) የሚሰጥ በመሆኑ፣ ፈጠራዎቹ የኢኖቬሽን ሥራዎችን ስለሚያጠናክሩና በዚህም ቀጣይነት ያለው የሰው ልጅ ሕይወት መሻሻልን የሚያረጋግጥ በመሆኑ እና በሌሎችም በጎ አስተዋጽዖዎች ፓተንት በዕጅጉ አስፈላጊ ነው ብለዋል። የንግድ ምልክት ምንድን ነው?፡- የንግድ ምልክት ማለት አንድን ምርት ወይም አገልግሎት ከሌላው ምርትና አገልግሎት እንዲለይ ለማስቻል በንግድ ምልክት ባለቤቶች ለምርታቸውና አገልግሎታቸው መለያ እንዲሆን ጥቅም ላይ የሚውል ልዩ ምልክት መሆኑን ተናግረዋል። የንግድ ምልክት ሸማቹ ሕብረተሰብ የሚፈልገውን ምርትና አገልግሎት በቀላሉ ለይቶ እንዲገዛ ከማስቻሉም በላይ በሚገዛው ምርትና አገልግሎት ጥራት ላይ በመተማመን ፍላጎቱን እንዲያሟላ ያደርጋል። የንግድ ምልክት ለባለመብቱ ምን ጥቅም ያስገኛል?፡- ምርቶቹ (አገልግሎቶቹ) በተጠቃሚዎች እንዲለዩለት ወይም እንዲታወቁለት ያደርጋል፣ ክፍያን መሠረት አድርጎ ሦስተኛ ወገን እንዲጠቀምበት የመፍቀድ፣ የንግድ ምልክቶች በራሳቸው ዋጋ አላቸው (የአዕምሯዊ ንብረት ዋጋ ትመና (IP Valuation) ለምሳሌ በፈረንጆቹ በ2026 የመጀመሪያ ወራት አፕል (Apple) 600 ቢሊየን ዶላር፣ ማይክሮሶፍት (Microsoft) 565 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር፣ ጉግል (Google) 433 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ዋጋ ግምት እንደነበራቸው ተብራርቷል። በተጨማሪም፤ የንግድ ምልክት በሕግ በሚቀመጥ የጊዜ ገደብ መሠረት እየታደሠ ለዘላለም ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል፤ የንግድ ምልክት ባለቤቱን በማስተዋወቅ ዕውቅናና የገንዘብ ትርፍን ያስገኛል፤ የንግድ ምልክት ተገቢ ያልሆኑ የንግድ ውድድሮችን በመግታት ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል (ተመሳስለው የሚሠሩና ለገበያ የሚቀርቡ ሥራዎችን (Counterfieited Products) ለመዋጋት ዓይነተኛ መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል፤ የንግድ ምልክት ሰዎች ምርቶቻቸውንና አገልግሎቶቻቸውን ሚዛናዊ በሆነ አግባብ እንዲያቀርቡ በማድረግና በብሔራዊና ዓለም አቀፍ ደረጃ የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት እንዲኖር ምቹ ሁኔታ በመፍጠር አስተዋጽዖው የላቀ ነው ብለዋል። ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ምንድን ነው?፡- ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ በምርቶች ሥነ-ውበት (Esthetics) ላይ ተመስርቶ ቅርጽን፣ መስመሮችን ወይም ቀለምን በመጠቀም ለገበያ የሚቀርቡ ምርቶች የገዥዎችን (ሸማቾችን) ቀልብ ለመሳብ እንዲችሉ በምርቶች ላይ የሚገለጽ የንድፍ ጥበብ ዘርፍ ነው ያሉት አቶ ብሩክ፤ ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች በኢንዱስትሪና ዕደ-ጥበብ ምርቶች ላይ ተዘጋጅተው ሊወጡና ለገበያ ሊቀርቡ ይችላሉ ይላሉ። ዘርፉ ከቴክኒካልና ሕክምና መሣሪያዎች አንስቶ እንደ ሠዓት፣ ጌጣጌጦችና ሌሎች የቅንጦት ምርቶች ዕቃዎችን ሊያካትት ይችላልም ብለዋል። የቤት ዕቃዎችን፣ የኤሌክትሪክ መሣሪያዎችን፣ ተሽከርካሪዎችና የሕንጻ ንድፎችን እንዲሁም የጨርቃጨርቅ ንድፍ ውጤቶች በኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ሥር የሚወድቁ ይሆናሉ ይላሉ። ኢንዱስትሪያዊ ንድፎች ጥበቃ የሚደረግላቸው አዲስ ወይም ወጥ ከሆኑ ብቻ መሆኑን ገልጸው፤ በዲዛይኑ ውስጥ ከሚገለጸው ምርት ጋር ተያያዥ የሆኑ የቴክኒክ ጉዳዮች ጥበቃ እንደማይደረግላቸው አስታውቀዋል። ለኢንዱስትሪያዊ ንድፍ ጥበቃ ማድረግ ለምን ያስፈልጋል?፡- በምርቶች ውበት ላይ የሚገለጽ በመሆኑ የተጠቃሚውን ዐይን ይስባል፣ የምርቶችን ዋጋ ይጨምራል፣ ፈጠራንና ውድድርን ያበረታታል፣ ለባለመብቱ ብቸኛ መብትን ያጎናጽፋል፣ በኢንዱስትሪዎች፣ ባሕላዊ ጥበብና በዕደ ጥበብ ዘርፍ ፈጠራ በማሻሻል ኢኮኖሚ እንዲያድግ ያደርጋል፣ የወጭ ንግድን (Export Trade) ያሳድጋል በማለት የኢንዱስትሪ ንድፍ ጥበቃ አስፈላጊነትን ያብራራሉ። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካች ምንድን ነው?፡- የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች በምርቶች ላይ የሚቀርቡ ምልክቶች ሆነው እነዚህ ምልክቶች አንድ የተወሰነ አካባቢን በምርቱ ምንጭነት የሚያመላክቱና ጥራትንና ዝናን ከቦታው ጋር አስተሳስረው የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን አቶ ብሩክ ያስረዳሉ። በአብዛኛው የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾች ልዩ ምርቱ የሚገኝበትን የቦታ ስም (Specific Local Geographyical Factors – Climate, Soil) ይይዛሉ። ለምሳሌ፡- Roquefort for Cheese -France፣ የማረቆ በርበሬ፣ የሸኖ ቅቤ፣ የዓድኣ ጤፍ … የመሳሰሉት ምርቶች ተጠቃሾች ናቸው። የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመላካቾችን መጠበቅ ለምን ያስፈልጋል?፡- ተጠቃሚዎች ምርቶች የሚገኙበትን ሀገር ወይም አካባቢ በቀላሉ ለመለየት፣ ሕጋዊነት በሌላቸው ወገኖች የምርቱ መገኛ አካባቢ እና የምርቱ ዝና በተሳሳተ መልኩ ለሌላ ምርት መጠሪያ እንዳይውል ለመከላከል ይረዳል ይላሉ። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምንድን ናቸው?፡- የቅጅ መብት በሥነ-ጽሑፍ እና ሥነ-ጥበብ ዘርፍ ወጥ የፈጠራ ሥራዎችን ለሚያመነጩ ደራስያን፣ አርቲስቶች ወዘተ… የባለቤትነት መብት የሚሰጥ የሕግ ማዕቀፍ መሆኑንም ነው ሥራ አስፈጻሚው የሚያስረዱት። በአንጻሩ ተዛማጅ የቅጅ መብት ማለት ይላሉ አቶ ብሩክ፤ በወጥ የፈጠራ ሥራዎች ላይ ተመስርተው የሚሠሩ ተዛማጅ (Related) የፈጠራ ሥራዎችን ያካትታል። ለምሳሌ፡- ከዋኞቹ (ተዋንያን እና ዘፋኞች)፣ ድምጽ ሪከርዲንግስ፣ አሳታሚዎች (ኮምፓክት ዲስኮች)፣ የብሮድካስት ተቋማት፣ (ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን) የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ ሲሉ ዘርዝረዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምን ዓይነት መብቶች ያስገኛሉ?፡- ባለመብቶች ሥራዎቻቸውን ለመጠቀም ወይም ሦስተኛ ወገኖች እንዲጠቀሙባቸው የመፍቀድ፣ ሥራዎች እንዲባዙ፣ ለሕዝብ እንዲዳረሱ፣ እንዲሠራጩ፣ እንዲተረጎሙ ወይም ወደሌላ ሥራ እንዲቀየሩ የመፍቀድ ወይም የመከልከል፣ የደራሲነት (የአመንጭነት) መብት ዕውቅና እንዲያገኙ፣ በብዕር ስም የመጠቀም መብት፣ ክብሩንና መልካም ስሙን የሚያጎድፍ የሥራ መዛባት እንዳይኖር የመጠበቅ ወይም የሥራው ወደሌላ መቀየር የሚያስከትለውን ጉዳት የመቃወም ወዘተ መብቶችን ያስገኛሉ ብለዋል። የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ምን ጥቅሞች ያስገኛል?፡- የሰውን ልጅ የፈጠራና ኢኖቬሽን ጥረቶችን ያሳድጋል፣ ለፈጠራ አመንጭዎች መበረታታትን ይፈጥራል፣ የሕጋዊ ተፈጻሚነትን በማረጋገጥ አመንጭዎችና በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች መዋዕለ-ነዋይ እንዲያፈሱ የፈጠራ ሥራዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚኖራቸውን የሥርጭት ሽፋን ያሳድጋል ነው ያሉት አቶ ብሩክ። የፓሪስ ስምምነት አባል ኢትዮጵያ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር ለመሆን ለዓለም አዕምሯዊ ንብረት ድርጅት (WIPO) ያስገባችው ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስምምነቱን ነሐሴ 9 ቀን 2017 ዓ.ም በማጽደቁ ከዚሁ ዕለት ጀምሮ ለስምምነቱ ተገዢ ሆናለች። አቶ ብሩክ እንዳብራሩት፤ የፓሪስ ስምምነት በጥቅሉ የኢንዱስትሪያዊ ንብረቶችን ጥበቃ የሚመለከት ነው። የፓተንት፣ የንግድ ምልክት፣ ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ፣ የግልጋሎት ሞዴል (በአንዳንድ ሀገራት ሕግ ኢትዮጵያን ጨምሮ “የአነስተኛ ፈጠራ የባለቤትነት መብት” በመባል የተደነገገ)፣ የአገልግሎት ምልክት፣ የንግድ ስም (የኢንዱስትሪ ወይም የንግድ እንቅስቃሴ የሚካሄድባቸው ስያሜዎች)፣ ጂኦግራፊያዊ አመላካች እና ፍትሐዊ ያልሆነ ውድድርን መከላከል ያካተተ ነው። የስምምነቱ መሠረታዊ ድንጋጌዎች በሦስት ዋና ዋና መርሆዎች እንደሚከፈሉ ጠቁመው፤ እነሱም፡- የፓሪስ ስምምነት አባል ሀገር መሆን በሌሎች አባል ሀገራት ውስጥ እንደ ዜጋ የመስተናገድ መብት፣ የቀዳሚነት መብት የማግኘት፣ በቀላሉ ዓለም አቀፍ ጥበቃ የማግኘት አሠራር እና መሰል ጉልህ ጥቅሞችን የማግኘት ዕድል ይሰጣል ሲሉ ይገልጻሉ። በመሠረቱ የፓሪስ ስምምነት የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃን በማቀላጠፍ አዳዲስ ግኝቶችንና ፈጠራዎችን እንዲሁም የንግድ ሥራዎች ድንበር ሳይገድባቸው የፓተንትና የንግድ ምልክት መብቶች በቀላሉ እንዲጠበቁ በማድረግ ፈጠራን፣ ንግድን እና ኢኮኖሚያዊ እድገትን እውን ያደርጋል ብለዋል። የዘንድሮው የአዕምሯዊ ንብረት ቀን የፊታችን ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም “አዕምሯዊ ንብረትና ስፖርት፤ እንዘጋጅ፣ እንጀምር፣ እንፍጠር!” በሚል መሪ ሐሳብ ዓለም አቀፉ የአዕምሯዊ ንብረት ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል። በስፖርት ዓለም ውስጥ የሚከሰቱ ተወዳዳሪዎች የግልና የጋራ ፈጠራዎች፣ ንድፎች፣ ብራንዶችና የመልካም ዝና ታሪኮችን ለመጠበቅና ሀገራትን ጭምር ለማስተዋወቅ የአዕምሯዊ ንብረት መብት ጥበቃ ሥርዓት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል። ምክንያቱም ስፖርት በባሕርይው በውድድር ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን፤ ከሀገራት ዝና፣ ከፋሽን ዲዛይን፣ ከመዝናኛ፣ ከሚዲያ ሥርጭት፣ ከጤናና ከዕለት ተዕለት መገልገያ ቁሶች ጋር የሚገናኝ በመሆኑ ነው።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 18, 2026 954
ከሚያዝያ 5 እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ በንፋስ ኃይል አማካኝነት ጨለማን ለመግፈፍ፣ ዐቅምን በለየ የቅድመ ጥናት እና ልዩ ዕቅድ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ዕውን አድርጋለች ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት 100 ሜጋ ዋት ንጹህ የኃይል አቅርቦት በመጨመር ወደ ዘርፈ-ብዙ እና ቀጣይነት ባለው የኃይል መጻዒ ዕጣ ፈንታ ለመገንባት የምናደርገውን ጉዞ ያጠናክረዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህም አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ አብነት ነው ብለዋል በወቅቱ። በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል፤ ከምንጊዜውም በላይ ታላቅ የምንሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉም አመላክተዋል። • ከኮፕ32 አስተናጋጅነት ጋር በተያያዘ ምክክር መደረጉ የኮፕ32 አስተናጋጇ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ መጀመሯን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል ሲሉ ገልጸዋል። ከግምገማ ባሻገር የቀጣይ አቅጣጫ መቀመጡን ጠቅሰው፤ ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልኅቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው ብለዋል። • የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከዚያም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በነበራቸው የሁለትዮሽ ውይይትም፤ ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ በቅኝ ያልተገዙ፣ ለአኅጉሩ ነፃነትና አንድነት ድምፅ በመሆን ከጋራ የጽናት ታሪክ የሚመነጭ ጥልቅና ዘመናትን የተሻገረ ግንኙነት አላቸው ያሉት ጠላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም እንደ ሁሌው ኢትዮጵያ ከሰፊ ገበታዋ ያላትን ታላቅ ዐቅምና ዘላቂ ወዳጅነት አብረዋት ለሚጓዙ ሁሉ ለማካፈል ዝግጁ ናት ብለዋል። ጉብኝቱም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን የቆየ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለማስፋት ወሳኝ ምዕራፍን ከፍቷል ሲሉ ገልጸዋል። ከሁለትዮሽ ስብሰባው በመቀጠልም በሁለቱ ሀገራት በኩል ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጉዞ ያካበተችውን ልምድ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ለማካፈል እንዲሁም ከአጋሮቻችን የተለያዩ ዕይታዎችን በመቅሰም ለአኅጉሩ ዕድገት ዘላቂና አፍሪካዊ መፍትሔዎችን በጋራ ለማፍለቅ እንደ ወሳኝ መሠረት ያገለግላሉ ነው ያሉት። • የፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ባሳለፍነው ሳምንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ቀጣይ ትብብሮችን በምናጠናክርባቸው ቁልፍ መስኮች ላይ መክረናል ብለዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም፤ ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ፣ የተሻገረ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ በበቂ ሁኔታ ዜጎችን ሥራ ለማስያዝ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሚና አይተኬ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ሥራ ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚ ያሸጋግራል፣ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሻገር እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ያገለግላል በማለት አብራርተዋል። በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነት አንዱ አንጓ ነው በማለት አስረድተዋል። የብዙ መንግሥታትና የእኛም ትኩረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ የሆነበት ዋናው ምክንያት፤ ኢንዱስትሪ ማደግ ለሚያስብ ሀገር በጣም ወሳኝ ነገር ስለሆነ ነው ብለዋል። አክለውም፤ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የኢኮኖሚ ልብ መሆኑን አስገንዝበዋል። አንድ ሰው ልቡ ካልሠራ ሌላው አካላቱ ጤነኛ ቢሆንም ውጤታማ እንደማይሆን ሁሉ፤ ኢኮኖሚን ኢኮኖሚ የሚያደርገው የኢኮኖሚ ልብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ነው ብለዋል። እንዲሁም የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል። የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግሥት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አብራርተዋል። ከተማ አያስፈልግኝም፤ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አመላክተዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በወሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገራችን በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ሥር እየሰደደ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሐሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል። እንዲሁም በ "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ሥራ ማስጀመራቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ማሳያ እና የወሎ የብልጽግና ተስፋ ነው ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የ"መደመር" ዕሳቤ በተግባር የታየበት፣ የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለ ሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት ነው ሲሉም ገልጸል። ያየነው ልማት የሰላም ውጤት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ በማለት፤ በአንድነት እና በትጋት ከሠራን ይህ ቀጣና የዕድገትና ብልጽግና መዳረሻ መሆኑ አይቀሬ ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና ኮንስትራክሽን ሳምንትን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት መሠረተ-ልማት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ግብዓቶችን በማመላለስ የኢኮኖሚያችን የደም ሥር፣ የብልጽግናችን መሠረት ነው ብለዋል። በዐውደ ርዕዩ የተመለከትነውም ወሳኝ የልማት ተቋሞቻችን፣ መሠረተ-ልማትን እንደ ሀገር በቅንጅትና በትብብር የመምራት አዲስ የሥራ ባህል እየገነቡ መሆናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል። መንግሥት በመንገድ፣ በኃይል፣ በመስኖ፣ በባቡርና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፍ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚሠራውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። አሁን ያለንበት ወቅት የሥራ፣ የውጤት እና የተስፋ ዘመን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ትናንት የተገነባው ለዛሬ፣ ዛሬ የምንገነባው ደግሞ ለነገው ትውልድ ኩራት እና የብልጽግና ዋስትና ነው ብለዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3919
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2674
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8461
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6949
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 108
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 544
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።