አርእስተ ዜና
ኢጋድ የሴቶች የመሬት ባለቤትነትና ውሳኔ ሰጪነት ሚና ለማሳደግ የሚደረጉ ጥረቶችን እንደሚደግፍ ገለጸ
Jul 12, 2025 13
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ሴቶች የመሬት ባለቤትነት መብታቸው እንዲከበር እና በአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎች ላይ የመሪነት ሚናቸው እንዲያድግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታወቀ። ኢጋድ ከሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም አንስቶ በኬንያ ናይሮቢ ስርዓተ ጾታ፣ መሬት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ግንባታ ላይ ሲያካሂድ የቆየው ቀጣናዊ ምክክር ዛሬ ተጠናቋል። በምክክሩ ላይ ሴት የፓርላማ አባላት፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት ተወካዮች፣ የቴክኒክ ባለሙያዎች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ሁነቱ የስርዓተ ጾታ እኩልነት፣ የመሬት አስተዳደር እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ግንባታ ላይ የሚሰሩ ተቋማትን በአንድ መድረክ ያገናኘ ነው። ውይይቱ የመሬት መብቶችን ማስጠበቅ እና ሴቶችን ያሳተፈ የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ላይ ሁሉን አቀፍ የፖሊሲ ምክክር ማድረግ እና ቀጣናዊ ትብብርን የማጠናከር ውጥን ያነገበ ነው።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ምክትል ዋና ፀሐፊ መሐመድ አብዲ ዋሬ ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር ምክክሩ ሴቶች በመሬት ባለቤትነት እና በአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችል ጠንካራ አቋም የተያዘበት መሆኑን አመልክተዋል። በቀጣናው የሚገኙ ሴቶች ለመሬት ልማት፣ ግብርና እና ለዜጎች ደህነት መጠበቅ ወሳኝ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ቢገኝም በመሬት ባለቤትነት እና ውሳኔ ሰጪነት ላይ ፈተናዎች እያጋጠሟቸው ነው ብለዋል። ሴቶችን ማብቃት ለፍትህ፣ እኩልነት እና ዘላቂ ልማት መረጋገጥ ቁልፍ እንደሆነ ተናግረዋል። የሴት ፓርላማ አባላት ቀጣናዊ ማዕቀፍ እና ቀጣናዊ የፖሊሲ ሰነድ ዝግጅት የውይይቱ ቁልፍ ውጤቶች ናቸው ብለዋል። የአሰራር ማዕቀፎቹ በመሬት መብቶች እና በማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ላይ ተግባራዊ ምላሽ መስጠት የሚያስችሉ እና የፖለቲካ ቁርጠኝነት የታየባቸው እንደሆነ አብራርተዋል። ሀገራት ቀጣናዊ ማዕቀፎቹን የብሄራዊ እቅዶቻቸው ጋር አጣጥመው እንዲተገብሩና ከቀጣናዊ የአሰራር ስርዓቶች ጋር ስራቸውን እንዲያስተሳስሩ ጥሪ አቅርበዋል። የፓርላማ አባላቱ የለውጥ መሐንዲሶች ናቸው ያሉት ምክትል ዋና ፀሐፊው ሴቶች የመሬት ባለቤት እንዲሆኑና በአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ የመሪነት ሚና እንዲኖራቸው አበክረው እንዲሰሩ ጠይቀዋል። ኢጋድ የሴቶችን የመሬት ባለቤትነት ለማረጋገጥ እና በማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ያላቸውን ሚና ለማሳደግ ቁርጠኛ እንደሆነ መግለጻቸውን ተቋሙ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ቀጣናዊ ምክክር ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳንና ዩጋንዳ የተካሄዱ ምክክሮች ማጠቃለያ ነው።
በአርባምንጭ ከተማ እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የብልጽግና ጉዞ ስኬት ማሳያ ናቸው - ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር)
Jul 11, 2025 62
አርባምንጭ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በአርባምንጭ ከተማ እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶች የብልጽግና ጉዞ ስኬት ማሳያ ናቸው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና አለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ገለጹ። የፌደራልና የክልሎች የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊዎች ማምሻውን የአርባምንጭ ከተማ ዓለም አቀፍ ስታዲየምና የከተማዋን የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴዎች ጎብኝተዋል። ከጉብኝት በኋላ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት በአርባምንጭ ከተማ እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የብልጽግና ጉዞ ስኬታማነት ማሳያ ናቸው።   በአምስት ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ስታዲየም ከሀገር አልፎ በአህጉር ደረጃ ትልቅ ፋይዳ ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ስታዲየሙ የአትሌቲክስ መሮጫና 25 ሺህ ሰው የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን የተለያዩ ጨዋታዎችን ማስተናገድ የሚችል ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን መመልከታቸውን ተናግረዋል። አክለውም በህብረተሰብ ተሳትፎና በመንግስት ትብብር እየተገነባ ያለው ስታዲየም የሀገሪቱን የእግር ኳስ ዕድገት ከፍ እንደሚያደርግ ያላቸውን እምነት ገለጸዋል። በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማትም በፓርቲው እሳቤ መሠረት ከተሞችን ጽዱና ውብ እንዲሁም ለህዝብ ምቹ የማድረግ ትልም መገለጫ ሆኖ ማግኘታቸውን ጠቁመዋል። የኮሪደር ልማቱ ለአርባምንጭ ከተማ ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ በመሆን ዘርፉን በማነቃቃት ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ ፋይዳ ያለው ነው ብለዋል።   ብልጽግና ፓርቲ በሁሉም የልማት መስኮች የህዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአርባምንጭ ከተማ መካሄዱ ይታወቃል።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው በተሻሻለው የኢትዮጵያ ምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። አዋጁ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚቀርብ ማንኛውም ቅሬታ በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት የሚደነግግ ሲሆን የምርጫ ክልል አቤቱታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት ከዚህ በፊት ከህብረተሰቡ ይመደብ የነበረው ቀርቶ ቦርዱ አሰልጥኖ በሚመድባቸው የምርጫ አስፈጻሚዎች እንዲተኩ የሚያደርግ ነው። ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ አንድ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመመዝገብ የሚመለምለው አባል ከ5 ክልሎች የነበረ ሲሆን በተሻሻለው አዋጅ አንድ ፓርቲ አባላትን መመልመል ያለበት ከ7 ክልሎች ሊሆን እንደሚገባም በአዋጁ ተመላክቷል። አንድ ፓርቲ ከመንግሥት ድጋፍ ለማግኘት ከ30 በመቶ ከሚሆነው አባሉ የአባልነት መዋጮ መሰብሰብ እንደቅደመ ሁኔታም ተቀምጧል። በአዋጁ መሰረት ጥሰት ፈጽመው የተገኙ ፓርቲዎች እስከ አምስት ዓመት ድረስ ሊታገዱ የሚችሉበት ድንጋጌም ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል ነው። በውይይቱ ከተሳተፉ መካከል የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ በምርጫ ጣቢያ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አይቶ ውሳኔ ይሰጣል የሚለው የአንቀጹ ክፍል ለአተገባበር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል ብለዋል።   የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ ባንዲራ በላቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲዎች 30 በመቶ መዋጮ እንዲያሰባስቡ የተቀመጠው ድንጋጌ ከነባራዊ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ወይ የሚለው ሊጤን እንደሚገባ ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው በአዋጁ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ድንጋጌዎች ሊካተቱ ይገባል ብለዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሌ በሰጡት ማብራሪያ በአዋጁ ፓርቲዎች 30 በመቶ ያህል መዋጮ ከአባላት ሊሰበሰቡ እንደሚገባ የተደነገገው ፓርቲዎች በመንግሥት በጀት ላይ ብቻ እንዳይመሰረቱና ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። አዋጁ አካል ጉዳተኞችንና ሴቶችን አካታች በሆነና ተሳትፏቸውን በሚያሳድግ መልኩ መቃኘቱን አንስተዋል። የመንግሥት ሰራተኞች በምርጫ ውድድር ወቅት ደሞዛቸውን ይዘው እንዲሳተፉ መደረጉ ለፖለቲካ ምህዳሩ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ነዋይ በሰጡት ማብራሪያ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚነሱ ቅሬታዎች በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ እንዲፈታ አቅጣጫ የተቀመጠው ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታልሞ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲያም ሆኖ ቅሬታዬ አልተፈታም የሚል ማንኛውም አካል ጥያቄውን በየደረጃው የሚያቀርብበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል።   በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራ አንደሞ በበኩላቸው በህዝባዊ የውይይት መድረኩ የተነሱ ሀሳቦች ለአዋጁ ውሳኔ ሀሳብ የሚረዱ ግበዓቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር ላይ የፓርቲዎች ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በበኩላቸው ፓርቲዎች የወጣቶችን፣ የአካል ጉዳተኞችንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የበለጠ ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአባልነት መዋጮን በተመለከተም ፓርቲዎች አባላቶቻቸውን ሊያበረታቱ እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን ስራ ላይ ለማዋል የጀመራቸውን ተግባራት ሊያጠናክር እንደሚገባ ጠቁመው ፓርቲዎችም ይሄንኑ ስራ ሊደግፉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
የሚታይ
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው በተሻሻለው የኢትዮጵያ ምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። አዋጁ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚቀርብ ማንኛውም ቅሬታ በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት የሚደነግግ ሲሆን የምርጫ ክልል አቤቱታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት ከዚህ በፊት ከህብረተሰቡ ይመደብ የነበረው ቀርቶ ቦርዱ አሰልጥኖ በሚመድባቸው የምርጫ አስፈጻሚዎች እንዲተኩ የሚያደርግ ነው። ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ አንድ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመመዝገብ የሚመለምለው አባል ከ5 ክልሎች የነበረ ሲሆን በተሻሻለው አዋጅ አንድ ፓርቲ አባላትን መመልመል ያለበት ከ7 ክልሎች ሊሆን እንደሚገባም በአዋጁ ተመላክቷል። አንድ ፓርቲ ከመንግሥት ድጋፍ ለማግኘት ከ30 በመቶ ከሚሆነው አባሉ የአባልነት መዋጮ መሰብሰብ እንደቅደመ ሁኔታም ተቀምጧል። በአዋጁ መሰረት ጥሰት ፈጽመው የተገኙ ፓርቲዎች እስከ አምስት ዓመት ድረስ ሊታገዱ የሚችሉበት ድንጋጌም ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል ነው። በውይይቱ ከተሳተፉ መካከል የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ በምርጫ ጣቢያ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አይቶ ውሳኔ ይሰጣል የሚለው የአንቀጹ ክፍል ለአተገባበር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል ብለዋል።   የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ ባንዲራ በላቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲዎች 30 በመቶ መዋጮ እንዲያሰባስቡ የተቀመጠው ድንጋጌ ከነባራዊ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ወይ የሚለው ሊጤን እንደሚገባ ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው በአዋጁ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ድንጋጌዎች ሊካተቱ ይገባል ብለዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሌ በሰጡት ማብራሪያ በአዋጁ ፓርቲዎች 30 በመቶ ያህል መዋጮ ከአባላት ሊሰበሰቡ እንደሚገባ የተደነገገው ፓርቲዎች በመንግሥት በጀት ላይ ብቻ እንዳይመሰረቱና ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። አዋጁ አካል ጉዳተኞችንና ሴቶችን አካታች በሆነና ተሳትፏቸውን በሚያሳድግ መልኩ መቃኘቱን አንስተዋል። የመንግሥት ሰራተኞች በምርጫ ውድድር ወቅት ደሞዛቸውን ይዘው እንዲሳተፉ መደረጉ ለፖለቲካ ምህዳሩ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ነዋይ በሰጡት ማብራሪያ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚነሱ ቅሬታዎች በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ እንዲፈታ አቅጣጫ የተቀመጠው ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታልሞ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲያም ሆኖ ቅሬታዬ አልተፈታም የሚል ማንኛውም አካል ጥያቄውን በየደረጃው የሚያቀርብበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል።   በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራ አንደሞ በበኩላቸው በህዝባዊ የውይይት መድረኩ የተነሱ ሀሳቦች ለአዋጁ ውሳኔ ሀሳብ የሚረዱ ግበዓቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር ላይ የፓርቲዎች ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በበኩላቸው ፓርቲዎች የወጣቶችን፣ የአካል ጉዳተኞችንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የበለጠ ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአባልነት መዋጮን በተመለከተም ፓርቲዎች አባላቶቻቸውን ሊያበረታቱ እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን ስራ ላይ ለማዋል የጀመራቸውን ተግባራት ሊያጠናክር እንደሚገባ ጠቁመው ፓርቲዎችም ይሄንኑ ስራ ሊደግፉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶች በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ እንዲገበያዩ መደረጉ የሪፎርም ስራዎችን የበለጠ ያጠናክራል - ሚኒስትር አህመድ ሽዴ
Jul 11, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶች በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ እንዲመዘገቡና እንዲገበያዩ መደረጉ የሪፎርም ስራዎችን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ። የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶችንና ሌሎች የሰነደ ሙዓለ ንዋዮችን የማገበያየት ሂደት በይፋ ጀምሯል።   በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ እንደተናገሩት ገበያው መጀመሩ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶችን በሰነደ መዋለ ነዋዮች አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ ለህዝብ ማቅረብ የሚያስችል ነው። አጠቃላይ የመንግስትን ፋይናንስ አስተዳደር የማዘመን ሪፎርምን ለማሳካት ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶች የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያዎች እንዲመዘገቡና እንዲገበያዩ መደረጉ የሪፎርም ስራዎችን የበለጠ ለማጠናከር ይረዳል ብለዋል። የተጠናቀቀው በጀት አመት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እያከናወነች ያለው የሪፎርም ስራ በስኬት የተጠናቀቀበት እንደሆነ በመግለጽ በቀጣይ በጀት አመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ጨረታዎች በገበያ መርሆች እንዲመሩ መደረጉን ተከትሎ የታዩት ለውጦች አበረታችና ውጤታማ ናቸው። እነዚህ ማሻሻያዎች የበጀት ጉድለትን ለመሙላት ከሚደረገው ጥረት በላይ ፋይዳ ያላቸው ሲሆኑ በኢኮኖሚው እንዲሁም በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ላይ ተአማኒነትና ተገማችነትን ለማስፋት የሚረዱ ናቸው።   የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ በበኩላቸው መንግስት ያጋጠሙ የምጣኔ ሃብት ችግሮችን በመፍታት የተረጋጋና ዘላቂ እድገት ማምጣት የሚያስችል ማሻሻያ ቀርጾ እየተገበረ መሆኑን አንስተዋል። ከእነዚህ መካከል ግልጽና ተአማኒነት ያለው የካፒታል ገበያ መገንባት አንዱ ሲሆን የዋጋ መረጋጋትን ለማምጣት፣ የገንዘብ ፖሊሲ መሳሪያዎች ውጤታማነትን ለማሳደግ ይረዳል ብለዋል። በተመሳሳይ ቁጠባና ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት፣ ከውጭ እዳ ጫና ጋር የሚገጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ ገበያው ትልቅ ሚና ይጫወታል ነው ያሉት።   የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃና ተኸልኩ የገበያው መጀመር ኢትዮጵያ በሀገር በቀል ምጣኔ ሃብት ማሻሻያው እያከናወነች ባለው ሁሉን አቀፍ ጠንካራና ገበያ መር ምጣኔ ሃብት ግንባታ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ገልጸዋል። ኢንቨስተሮች በገበያው ላይ በንቃት መሳተፍ የሚችሉበትን እድል የፈጠረና የመንግስት የእዳ አስተዳደር የማዘመን ሂደት ላይም ትልቅ አስተዋጽኦ የሚኖረው እርምጃ እንደሆነ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሰነደ ሙዓለ ነዋዮች የገበያ መድረክ ሲሆን በመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት የተቋቋመ ነው። የገበያው ዋና ዓላማ ውጤታማ የካፒታል ማሰባሰብ ስራዎችን በማጠናከር የኢትዮጵያን ምጣኔ ሃብት እድገት ግልጽና ደህንነቱ በተጠበቀ የካፒታል ገበያ ስራዎች መደገፍ ነው።    
በመዲናዋ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን 219 በማድረስ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ ተደርጓል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 11, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦በ2017 በጀት ዓመት በመዲናዋ የገበያውን ሁኔታ ለማረጋጋት የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎችን 219 በማድረስ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች በቀጥታ እንዲደርስ መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። 3ኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ እና የበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ ስብሰባ የመጀመሪያ ቀን ውሎ ተካሂዷል። በስብሰባው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና አቅጣጫዎች ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።   በከተማዋ ሰላምና ጸጥታ፣ በተቋማት ሪፎርም፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በመሰረተ ልማትና በማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች የተከናወኑ ተግባራትን ዝርዝር ሪፖርት አቅርበዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት በበጀት ዓመቱ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል አቅም በተቋማት መፈጠሩን አንስተዋል። 347 አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በመከላከል በተቋማት ውስጥ ግልጽነት እንዲፈጠርና የተገልጋይ እንግልት እንዲቀንስ መደረጉን ገልጸዋል። ይሁንና በአንዳንድ ተቋማት አሁንም ቢሆን በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች በመኖራቸው የማስተካከያ እርምጃ በመወሰድ ላይ ነው ብለዋል። በበጀት ዓመቱ በሌብነትና ብልሹ አሰራር የተሳተፉ አመራርና ሠራተኞች ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸው፥ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የትምህርት ቤቶችንና የጤና ተቋማትን ደረጃ በማሻሻልና አዳዲስ በመገንባት እንዲሁም የምገባ ማዕከላትን በማስፋት ትውልድ ላይ ውጤታማ ስራዎች መሰራቱንም ከንቲባዋ አብራርተዋል። በበጀት ዓመቱ በከተማ ግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች ለ336 ሺህ የከተማዋ ሥራ ፈላጊዎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ከንቲባዋ አንስተዋል። በበጀት ዓመቱ ከተማዋን ከጎበኙ አንድ ሚሊዮን የውጭ ቱሪስቶች 143 ቢሊዮን ብር በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ወደ ኢኮኖሚው ፈሰስ መደረጉን አመልክተዋል። በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን 9 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሀገር ወስጥ ጎብኚዎች ተዘዋውረው እንደጎበኟቸው እና በርካታ ገቢ እንዳስገኙም አንስተዋል። በሌላ በኩል የገበያውን ሁኔታ ለማረጋጋትና የኑሮ ወድነቱን ለማቃለል ከተማ አስተዳደሩ ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ለተለያዩ ዘርፎች በመመደብ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረጉን ነው የገለጹት። አዳዲስ የገበያ ማዕከላትን በማስፋፋት እና የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎችን 219 በማድረስ አምራቾች በቀጥታ ምርቶቻቸውን ለነዋሪዎች በተመጣጠኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚህም የገበያ ሰንሰለቱን በማሳጠር አምራቹንም ሸማቹንም ተጠቃሚ አድርገናል ነው ያሉት። በትራንስፖርት፣ በጤና መድህን፣ በዳቦ ምርትና በምገባ አቅርቦትን በመጨመር የኑሮ ጫናውን የሚያቃልሉ ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። የገቢ አሰባሰብን በማሳደግ እና ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድም በበጀት ዓመቱ ስኬት መመዝገቡን ከንቲባዋ ተናግረዋል። በከተማ አስተዳደሩ፣ በባለሃብቱ እና በህብረተሰብ ተሳትፎ በርካታ የልማት ሥራዎችና የስፖርት ማዘወተሪያና የህጻናት መጫወቻ ስፍራዎች መሰራታቸውን አስገንዝበዋል። ከተማ አስተዳደሩ የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን በማስቀጠል በአዲሱ በጀት ዓመት በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።          
የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች ለሀገር እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መደላድል ይፈጥራል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ያላቸውን ሚና በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መደላድል እንደሚፈጥር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። ቋሚ ኮሚቴው የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት የባለድርሻ አካላት አስረጂ መድረክ አካሂዷል።   የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ቤተልሔም ላቀው(ዶ/ር) ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ በቋሚ ኮሜቴው የተዘጋጁ ጥያቄዎችን በዝርዝር አቅርበዋል። በረቂቅ አዋጁ የተካተቱ አንቀጾች ላይ የሚስተዋሉ የግልጽነትና የትርጓሜ ለውጥ የሚያመጡ ሃሳቦች በድጋሚ ሊፈተሹ እንደሚገባ አንስተዋል። እንዲሁም የረቂቅ አዋጁን የህግ ማዕቀፍ ዝግጅት፣ የአጋር አካላት ሚና እና የአዋጁን አስፈላጊነት በሚመለከት ማብራሪያ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር)፤ ከቋሚ ኮሚቴው ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በምላሻቸውም ረቂቅ አዋጁ እንደሀገር የሃብት ምንጭ የሆኑ አዳዲስ አማራጮችንና አሰራሮችን ለማስፋት ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል። በዋናነት መንግስት የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለውን ተግባር ''ከሃሳብ እስከ አምራችነት'' የሚለውን እሳቤ የሚደግፍ መሆኑንም አንስተዋል። ረቂቅ አዋጁ የወጣቱን አምራችነት ለማሳደግ እንዲያግዝ ታልሞ በጥንቃቄ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመው፥ ለዚህም አስቻይ የሆኑ የህግ ማዕቀፎችን ለማካተት ጥረት ተደርጓል ነው ያሉት። ቋሚ ኮሚቴው ረቂቅ አዋጁን በሚመለከት የሰጠው ግብረ መልስ ጉድለቶችን ለማረምና ለመፈተሽ የሚያግዝ በመሆኑ የቀጣይ የቤት ስራ በማድረግ የመፈተሽ ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ረቂቅ አዋጁ ሀገሪቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላትን የማምረት አቅም ለማጉላት እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በተጨማሪም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያለው አበርክቶ የጎላ መሆኑን ገልጸው፤ በእውቀትና ፈጠራ የተመሰረተ ኢኮኖሚ ለመገንባት አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቁመዋል። ረቂቅ አዋጁን ይበልጥ ለማዳበር ስታርታፖችንና ባለድርሻ አካላትን በቅርበት የማወያየትና ግብዓት የማሰባሰብ ስራ መከናወኑን ጠቁመዋል።   በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በሰጡት ማጠቃለያ፤ የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ለአካታች ኢኮኖሚ ግንባታ አስቻይ ሁኔታን እንደሚፈጥር አብራርተዋል። ረቂቅ አዋጁ ኢትዮጵያ ያላትን የወጣት ኃይል በተገቢው መልኩ ለመጠቀምና የፈጠራ ሃሳብ ጥቅም ላይ እንዲውል ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። የተለያየ የፈጠራ ሃሳብ፣ ችሎታና በቴክኖሎጂ የዳበረ እውቀት ያላቸው ስታርታፖች በመረጡት መስክ ተሰማርተው ከሀገር አልፎ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አዋጁ አዎንታዊ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል። የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ያላቸውን ሚና በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በይፋ ግብይት ጀመረ
Jul 11, 2025 160
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በይፋ ግብይት ጀምሯል። ይፋዊ የግብይት ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የባንክ ፕሬዝዳንቶችና የልማት አጋሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው። የወጋገን እና የገዳ ባንኮች በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ሰነዶቻቸውን በማስመዝገብና ሌሎች መስፈርቶችን በማሟላት ግብይታቸውን በይፋ አስጀምረዋል። የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ግብይት መጀመሩ፥ የሪፎርም ስራዎችና የግሉ ዘርፍ ስኬት መሆኑን ተናግረዋል። ገበያው ኢኮኖሚውን የበለጠ በማነቃቃት፣ የበጀት ጉድለትን ለመሸፈንና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት አስረድተዋል። እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ የገበያው መጀመር ኢንቨስተሮች ለረጅም ጊዜ ሲጠይቁት የነበረ በመሆኑ አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን የሚከፍት ነው። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አጠቃላይ የኢኮኖሚ ማሻሻያ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸው በቀጣይ ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት። የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ፥ መንግስት በኢኮኖሚው ውስጥ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል ጠንካራ የካፒታል ገበያ መመስረት አንዱ መሆኑን አንስተዋል። የገበያው መጀመር የዋጋ መረጋጋትን ለማምጣትና ቁጠባን ለማበረታታት ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸው በቀጣይ ገበያውን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጥላሁን ካሳሁን(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ገበያው አስፈላጊ ዝግጅቶችና ሒደቶችን አልፎ በይፋ ግብይት መጀመሩን ገልጸዋል። የግብይቱ መጀመር ለሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነም ተነግሯል። የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሰነደ ሙዓለ ነዋዮች የገበያ መድረክ ሲሆን በመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት የተቋቋመ ነው። የገበያው ዋና ዓላማ ውጤታማ የካፒታል ማሰባሰብ ስራዎችን በማጠናከር የኢትዮጵያን ምጣኔ ሃብት እድገት ግልጽና ደህንነቱ በተጠበቀ የካፒታል ገበያ ስራዎች መደገፍ ነው።  

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው በተሻሻለው የኢትዮጵያ ምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። አዋጁ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚቀርብ ማንኛውም ቅሬታ በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት የሚደነግግ ሲሆን የምርጫ ክልል አቤቱታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት ከዚህ በፊት ከህብረተሰቡ ይመደብ የነበረው ቀርቶ ቦርዱ አሰልጥኖ በሚመድባቸው የምርጫ አስፈጻሚዎች እንዲተኩ የሚያደርግ ነው። ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ አንድ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመመዝገብ የሚመለምለው አባል ከ5 ክልሎች የነበረ ሲሆን በተሻሻለው አዋጅ አንድ ፓርቲ አባላትን መመልመል ያለበት ከ7 ክልሎች ሊሆን እንደሚገባም በአዋጁ ተመላክቷል። አንድ ፓርቲ ከመንግሥት ድጋፍ ለማግኘት ከ30 በመቶ ከሚሆነው አባሉ የአባልነት መዋጮ መሰብሰብ እንደቅደመ ሁኔታም ተቀምጧል። በአዋጁ መሰረት ጥሰት ፈጽመው የተገኙ ፓርቲዎች እስከ አምስት ዓመት ድረስ ሊታገዱ የሚችሉበት ድንጋጌም ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል ነው። በውይይቱ ከተሳተፉ መካከል የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ በምርጫ ጣቢያ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አይቶ ውሳኔ ይሰጣል የሚለው የአንቀጹ ክፍል ለአተገባበር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል ብለዋል።   የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ ባንዲራ በላቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲዎች 30 በመቶ መዋጮ እንዲያሰባስቡ የተቀመጠው ድንጋጌ ከነባራዊ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ወይ የሚለው ሊጤን እንደሚገባ ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው በአዋጁ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ድንጋጌዎች ሊካተቱ ይገባል ብለዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሌ በሰጡት ማብራሪያ በአዋጁ ፓርቲዎች 30 በመቶ ያህል መዋጮ ከአባላት ሊሰበሰቡ እንደሚገባ የተደነገገው ፓርቲዎች በመንግሥት በጀት ላይ ብቻ እንዳይመሰረቱና ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። አዋጁ አካል ጉዳተኞችንና ሴቶችን አካታች በሆነና ተሳትፏቸውን በሚያሳድግ መልኩ መቃኘቱን አንስተዋል። የመንግሥት ሰራተኞች በምርጫ ውድድር ወቅት ደሞዛቸውን ይዘው እንዲሳተፉ መደረጉ ለፖለቲካ ምህዳሩ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ነዋይ በሰጡት ማብራሪያ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚነሱ ቅሬታዎች በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ እንዲፈታ አቅጣጫ የተቀመጠው ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታልሞ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲያም ሆኖ ቅሬታዬ አልተፈታም የሚል ማንኛውም አካል ጥያቄውን በየደረጃው የሚያቀርብበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል።   በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራ አንደሞ በበኩላቸው በህዝባዊ የውይይት መድረኩ የተነሱ ሀሳቦች ለአዋጁ ውሳኔ ሀሳብ የሚረዱ ግበዓቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር ላይ የፓርቲዎች ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በበኩላቸው ፓርቲዎች የወጣቶችን፣ የአካል ጉዳተኞችንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የበለጠ ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአባልነት መዋጮን በተመለከተም ፓርቲዎች አባላቶቻቸውን ሊያበረታቱ እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን ስራ ላይ ለማዋል የጀመራቸውን ተግባራት ሊያጠናክር እንደሚገባ ጠቁመው ፓርቲዎችም ይሄንኑ ስራ ሊደግፉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት ይሰራል - አቶ ፍቃዱ ተሰማ
Jul 11, 2025 72
ጎንደር፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ። ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የተውጣጡ የፓርቲው የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች የተሳተፉበትና በጎንደር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የግምገማ መድረክ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ማምሻውን ተጠናቋል። አቶ ፍቃዱ ተሰማ የግምገማ መድረኩ ማጠቃለያን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ ፓርቲው መጪው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን መላ አባላቱን የማዘጋጀት ስራዎቹን በትኩረት ያከናውናል ብለዋል። ለዚህም የአባላት የስነ-ምግባር ደንቦችን በማዘጋጀት በምርጫው የትብብርና ፉክክር ዴሞክራሲያዊ ባህል እንዲዳብር እንደሚሰራም ተናግረዋል። አባላቱ በፓርቲው እሳቤዎች፣ መተዳደሪያ ደንብና አሰራሮች ዙሪያ ወጥና የተቀራረበ ግንዛቤ በመያዝ ተቋማዊ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ አቅማቸውን የመገንባት ስራ ይከናወናል ብለዋል። የፓርቲው አደረጃጀቶች በልማት በሠላምና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል እንደሚሰሩም ጠቁመዋል። የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደፓርቲና መንግስት ሰፋ ያሉ ውጤቶች የተመዘገቡበትና የማንሰራራት ዘመን በተጨባጭ የታየበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዓመቱ በፓርቲው ውስጥ የአመለካከት፣ የተግባር አንድነትና ህብረ ብሔራዊነት የተጠናከረበት እንደነበርም ተናግረዋል። ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚደረገው ጥረት በጎ ጅምር የታየበት፣ ኢኮኖሚያዊ እድገቱ የሀገሪቱን በጀት በትሪሊዮን እንዲጸድቅ ያስቻለና የእዳ ቅነሳ የተደረገበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራና የከተሞች ኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤታማ እንደነበርም አብራርተዋል፡፡ በሠላም ማስከበር ሂደቱ የታጠቁ ኃይሎች የመንግስትን የሠላም አማራጭ ተቀብለው ተሃድሶ በመውሰድ በስፋት ወደ ሠላማዊ ህይወት መመለሳቸውንም አስታውሰዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳካ ፓርቲው የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ኃላፊው አረጋግጠዋል።
በበጀት አመቱ በከተማዋ በተከናወኑ ስኬታማ የሰላም ተግባራት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ ነበር - የከተማዋ የምክር ቤት አባላት
Jul 11, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት አመቱ በከተማዋ በተከናወኑ ስኬታማ የሰላም ተግባራት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበር የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። 3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ እና የበጀት አመቱ ማጠቃለያ ስብሰባ እየተካሄደ ነው። በስብሰባው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና አቅጣጫዎችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። በዚሁ ጊዜ በ2017 በጀት ዓመት የከተማዋን ሰላም በማስጠበቅ፣ የነዋሪዎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ እንዲሁም አህጉራዊና ዓለም-አቀፋዊ ሁነቶችን በማስተናገድ ስኬታማ ሥራዎች መሰራታቸውን ነው ያብራሩት። በከተማዋ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በርካታ የጸጥታና የወንጀል ድርጊቶችን በመለየትና አስቀድሞ በመከላከል ብሎም ህጋዊ እርምጃዎችን መውሰድ መቻሉን አንስተዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላትም የከተማዋን ሰላምና ደህንነት ከማረጋገጥ አንጻር የተከናወኑት ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊና የምክር ቤቱ አባል ሊዲያ ግርማ በበጀት ዓመቱ በከተማዋ ሰላም በመረጋገጡ የልማት ስራዎች ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲከናወኑ በትኩረት መሰራቱን ገልጸዋል። የከተማው ነዋሪ ህብረተሰብም በወንጀል መከላከል ሂደትና ሰላም በማስጠበቅ ሂደት ላይ የነበረው ተሳትፎ በየጊዜው እየጎለበተ መምጣቱን እንዲሁ። ሰላም ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ልማት የማይተካ ሚና አለው ያሉት ደግሞ ሌላዋ የምክር ቤት አባል ወርቅነሽ ምትኩ (ዶ/ር) ናቸው።   በከተማዋ ለተመዘገቡ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጦች የሰላምና ጸጥታ መረጋገጥ ትልቅ ሚና መጫወቱንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ ሌላው የምክር ቤት አባል ኢቲሳ ደሜ(ዶ/ር) ህዝብን ያሳተፈ የሰላምና ልማት ሥራ የተሻለ ውጤት እንደሚያመጣ አዲስ አበባ ማሳያ ናት ብለዋል።   ከተማዋ የአህጉራዊና አለም አቀፋዊ ተቋማት መቀመጫና የአፍሪካ መዲና በመሆኗ ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ በኩል ህብረተሰቡ ቀጣይነት ያለው ድጋፉንና ተሳትፎውን ማስቀጠል እንደሚገባ በመጥቀስ። በከተማዋ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንዲረጋገጡ የምክር ቤቱ አባላት ድጋፍና ክትትላቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። የከተማዋን ሰላም በማስቀጠል ሂደትም ነዋሪው ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥል የምክር ቤት አባላቱ ጥሪ አቅርበዋል።
በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ በውጤታማነት ተጠናክሮ ቀጥሏል - ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)
Jul 11, 2025 89
አርባምንጭ ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ) ፡-በሀገሪቱ በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ በውጤታማነት ተጠናክሮ መቀጠሉን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ተናገሩ ። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተገመገመ ነው። የብልጽግና ፓርቲ ዓለም አቀፍና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ በኢኮኖሚው በፖለቲካውና፣ በዲፕሎማሲው ዘርፍ በዓለም አደባባይ ፈጣን ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች ብለዋል። ይህን ለማሳካትም የተረጋጋ የፖለቲካ ምህዳር በመፍጠር በህዝቦች መካከል ወንድማማችነትና እህትማማችነት እየተጠናከረ የመጣበት ዓመት ነው ሲሉም ገልጸዋል።   የሀገርን እድገት ወደ ኋላ ለመመለስ የሚጥሩ አካላት በህዝብና በመንግስት ትብብር ሴራቸው እየከሸፈ መምጣቱንም ገልጸዋል። በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ ሂደትም ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ያነሱት ቢቂላ (ዶ/ር) ''እስካሁን የተመዘገበውን ስኬት ለማስቀጠል አበክረን እንሠራለን'' ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው ፓርቲው የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል።   የብሔር ብሔረሰቦችን መብት በማስከበር የተረጋጋች ሀገር የመገንባት ሂደቱም በተሻለ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። በቀጣይም የተጀመሩ ልማቶችን በማስቀጠል የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ጠቁመዋል። ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው መድረክ ከሁሉም ክልሎች የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤታማ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገሩ ተግባር ይጠናከራል
Jul 10, 2025 116
  ሐረር፤ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)፡-በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤታማ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ በሐረር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲያካሂደው የቆየው የ2017 እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 እቅድ ተግባቦት መድረክ ዛሬ ተጠናቋል። በመድረኩ የፌደራልና የክልል የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ አመራሮች እንዲሁም የፓርቲው የወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ተሳትፈዋል። በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ በ2017 በጀት ዓመት የዴሞክራሲ ባህል እሴትን ለማጠናከር የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።   የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር ከመስራት አንጻር በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በጋራ ምክር ቤቶች በመደራጀት አብሮ የመስራት ባህል እየዳበረ መምጣቱን ጠቅሰዋል። ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የተጀመሩ ስራዎች አዲስ ባህልና ልምድ እያመጡ ስለመሆኑም አንስተዋል። የጋራ ስራዎቹ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በቁርጠኝነት መስራታቸውን አጎልብተው እንዲቀጥሉም አመልክተዋል። በአሁኑ ወቅት በየደረጃው ያለው የመንግስት አካላትና ሲቪል ማህበረሰብ በጋራና በቅንጅት የሚሰሩበት ጅምር ሁኔታ መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በተለይ የወጣቶችና ሴቶች አስተዋጽኦን ለማላቅና ተሳትፏቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ብሎም ተጠቃሚነታቸውን ለማጎልበት መድረኩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አንስተዋል።   በቀጣይም ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሰረት ትኩረት ተሰጥቶ እና ባህል አድርጎ እንደሚሰራም አመላክተዋል።
የከተማው ነዋሪዎች ሰላምን ለማፅናት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Jul 10, 2025 111
ደብረብርሃን ፤ ሐምሌ 3/ 2017 (ኢዜአ)፡- የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንደገለጹት፤ የጸጥታ ሃይሉ ከሕብረተሰቡ ጋር በመተባበር ሰላም እንዲከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።   በዚህም በከተማዋ የሚካሄዱ የኢንዱስትሪ፣ የኢንቨስትመንትና የንግድ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቅሰዋል። ይህም ስራ እድል እንዲስፋፋ፣ የገቢና ሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ እንዲሆኑ ምቹ መደላድል መፍጠሩን ገልጸዋል። በከተማዋ አሁን ላይ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተካሄዱ እንደሚገኙ አስረድተዋል። የልማት ሁሉ መሰረት የሆነውን ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ሁሉ ሕብረተሰቡ ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የተለመደ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላልፈዋል። የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብሩ ዓላማም የከተማው ነዋሪዎች ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የህግ ማስከበር ስራው ይበልጥ በውጤታማነት በማስቀጠሉ ሂደት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ለማበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።   ከህግ አስከባሪዎች መካከል ሀምሳ አለቃ ሰይፈ ደምሰው በሰጡት አስተያየት፤ ሰላምን አፅንቶ በማስቀጠል ለልማት የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ይበልጥ ለማጠናከር ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀናጅተወ በትኩረት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ሌላው የመርሃ ግብሩ ተሳታፊ ፈለቀ በየነ በበኩላቸው፤ የአካባቢውን ሰላም በማፅናት የልማት ስራዎቻቸው ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጎዳና ላይ ትርኢቶችና ሌሎች ዝግጅቶች ተካሂደዋል።
በብሔረሰብ አስተዳደሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል
Jul 10, 2025 95
ሰቆጣ ፤ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት መከናወናቸውን የብሔረሰብ አስተዳደሩ አስታወቀ። የብሔረሰብ አስተዳደሩ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምን የሚገመግምና የቀጣይ 90 ቀናት ዕቅድ ማስተዋወቂያ መድረክ በሰቆጣ ከተማ እየተካሄደ ነው። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሃይሉ ግርማይ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላምና ፀጥታ ተግባር በመካሄዱ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል።   በልማት ሥራም ለመልካም አስተዳደር ምክንያት ሆኖ የቆየው የሰቆጣ አዳሪ ትምህርት ቤትን ጨምሮ የስርዓተ ምግብን ለማሻሻል በዓመት ከ360 ሺህ በላይ ጫጩት ማስፈልፈያ ማዕከል ግንባታ ስራን ማከናወን እንደተቻለ ገልጸዋል። በተጨማሪም የመስኖ መሰረተ ልማትን በማስፋፋት የግብርና ምርታማነት እንዲያድግ መሰራቱን ጠቁመው፣ የመኽር እርሻ ምርታማነትን ለማሳደግም በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። በፌደራል፣ በክልልና በወረዳ በጀት እየተገነቡ ያሉ መሰረተ ልማቶች በተቀመጠላቸው ጊዜ በጥራት ተገንብተው እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትሉ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የአመራሩን የማስፈፀም አቅም ይበልጥ በማሳደግ በበጀት ዓመቱ የተገኙ ስኬቶችን በአዲሱ በጀት ዓመትም ለመድገም ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አቶ ሃይሉ አስረድተዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ጭምር ያልተቋረጠ የጤና አገልግሎት መስጠት መቻሉን የተናገሩት ደግሞ የብሔረሰብ አስተዳደሩ ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ ናቸው።   በበጀት ዓመቱ በስርዓተ ምግብ ማሻሻል እንዲሁም የወባ እና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን በመከላከልና በማከም በተሰራው ስራም የከፋ ችግር ሳይደርስ ማለፉንም ተናግረዋል። የእናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከልን ጨምሮ 42 የጤና ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆናቸውን የተናገሩት አቶ አሰፋ፤ በጤና ተቋማቱ ዜጎችን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል። የብሄረሰብ አስተዳደሩ የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ በበኩላቸው "በብሔረሰብ አስተዳደሩ በመስኖ ከለማው መሬት ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል ብለዋል። ይህም የአካባቢውን ገበያ ለማረጋጋት ማገዙን ተናግረዋል።   በበጋው ወቅት በ369 ተፋሰሶች ላይ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ መካሄዱን ጠቁመው፣ የለሙትን ተፋሰሶች በስነ እፅዋት ዘዴ ለማጠናከርም ችግኞች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ የክልል፣ የብሔረሰብ አስተዳደሩና የወረዳ አመራሮች ተሳትፈዋል።
የኢትዮጵያና ዛምቢያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በተለያዩ መስኮች ተጠናክሮ ቀጥሏል - አምባሳደር ሮዝ ሳካላ
Jul 10, 2025 122
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እና በዛምቢያ መካከል ያለው ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ግንኙነት በተለያዩ መስኮች ተጠናክሮ መቀጠሉን በኢትዮጵያ የዛምቢያ አምባሳደር ሮዝ ሳካላ ገለጹ። በኢትዮጵያ የዛምቢያ አምባሳደር ሮዝ ሳካላ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ እና ዛምቢያ ዘላቂ እና ዘርፈ-ብዙ ግንኙነት እንዳላቸው ገለጸዋል። ይህም ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እና በተለያዩ ዘርፎችም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። በተለይም ዛምቢያ ኤምባሲዋን በኢትዮጵያ ከከፈተችበት ጊዜ አንስቶ የሁለቱ አገሮች አጋርነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ ከመምጣቱም በላይ የተለያዩ የትብብር ስራዎችም እየተጠናከረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እ.አ.አ በ2017 ሁለቱ ሀገራት የጋራ ኮሚሽን ማቋቋማቸውን ገልጸው፤ ይህም ተጨባጭ ጥቅሞችን ማስገኘቱን ጠቁመዋል። ሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ አቅም እንዳላቸው ገልጸው፤ ከሁለቱም ወገኖች የተውጣጡ የንግድ ባለሙያዎችን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማሰባሰብ ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማሳደግ ጥረት መደረጉን አንስተዋል። የጋራ ኮሚሽኑ በንግድና ኢንቨስትመንት በተለይም በግብርናና በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትስስር እንደሚያጠናክር ጠቁመዋል። ዛምቢያ የአፍሪካን አንድነት ለማጎልበት እና አህጉራዊ አጀንዳዎችን ለማራመድ በተለያዩ መድረኮች በማደራጀት እና በመሳተፍ ንቁ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑን ተናግረዋል ። አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ ቋሚ ውክልና አለማግኘቷ ኢ-ፍትሃዊ ነው ብለዋል። ዛምቢያ ለቀጣናው ኢኮኖሚያዊ ውህደት ትልቅ አስተዋፅዖ እንዳደረገች ገልፀው፤ ፓን አፍሪካኒዝም እንደ መሰረታዊ መርህ እና ከእነዚህ ጥረቶች ጀርባ አንቀሳቃሽ ሃይል ሆኖ ያገለግላል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ለአፍሪካ በርካታ እድሎችን የሚሰጥ ወርቃማ አጀንዳ መሆኑን ገልጸው፤ በትብብር መተግበር እንደሚገባ አሳስበዋል።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 103
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው በተሻሻለው የኢትዮጵያ ምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ማህበራት፣ መገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። አዋጁ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚቀርብ ማንኛውም ቅሬታ በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት የሚደነግግ ሲሆን የምርጫ ክልል አቤቱታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት ከዚህ በፊት ከህብረተሰቡ ይመደብ የነበረው ቀርቶ ቦርዱ አሰልጥኖ በሚመድባቸው የምርጫ አስፈጻሚዎች እንዲተኩ የሚያደርግ ነው። ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ አንድ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመመዝገብ የሚመለምለው አባል ከ5 ክልሎች የነበረ ሲሆን በተሻሻለው አዋጅ አንድ ፓርቲ አባላትን መመልመል ያለበት ከ7 ክልሎች ሊሆን እንደሚገባም በአዋጁ ተመላክቷል። አንድ ፓርቲ ከመንግሥት ድጋፍ ለማግኘት ከ30 በመቶ ከሚሆነው አባሉ የአባልነት መዋጮ መሰብሰብ እንደቅደመ ሁኔታም ተቀምጧል። በአዋጁ መሰረት ጥሰት ፈጽመው የተገኙ ፓርቲዎች እስከ አምስት ዓመት ድረስ ሊታገዱ የሚችሉበት ድንጋጌም ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል ነው። በውይይቱ ከተሳተፉ መካከል የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ መብራቱ ዓለሙ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ በምርጫ ጣቢያ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አይቶ ውሳኔ ይሰጣል የሚለው የአንቀጹ ክፍል ለአተገባበር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል ብለዋል።   የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ ባንዲራ በላቸው እንደገለጹት፤ ፓርቲዎች 30 በመቶ መዋጮ እንዲያሰባስቡ የተቀመጠው ድንጋጌ ከነባራዊ ሁኔታ አኳያ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ወይ የሚለው ሊጤን እንደሚገባ ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው በአዋጁ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ድንጋጌዎች ሊካተቱ ይገባል ብለዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሌ በሰጡት ማብራሪያ በአዋጁ ፓርቲዎች 30 በመቶ ያህል መዋጮ ከአባላት ሊሰበሰቡ እንደሚገባ የተደነገገው ፓርቲዎች በመንግሥት በጀት ላይ ብቻ እንዳይመሰረቱና ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። አዋጁ አካል ጉዳተኞችንና ሴቶችን አካታች በሆነና ተሳትፏቸውን በሚያሳድግ መልኩ መቃኘቱን አንስተዋል። የመንግሥት ሰራተኞች በምርጫ ውድድር ወቅት ደሞዛቸውን ይዘው እንዲሳተፉ መደረጉ ለፖለቲካ ምህዳሩ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ነዋይ በሰጡት ማብራሪያ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የሚነሱ ቅሬታዎች በምርጫ ጣቢያ ኃላፊ እንዲፈታ አቅጣጫ የተቀመጠው ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታልሞ መሆኑን አስረድተዋል። እንዲያም ሆኖ ቅሬታዬ አልተፈታም የሚል ማንኛውም አካል ጥያቄውን በየደረጃው የሚያቀርብበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል።   በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አዝመራ አንደሞ በበኩላቸው በህዝባዊ የውይይት መድረኩ የተነሱ ሀሳቦች ለአዋጁ ውሳኔ ሀሳብ የሚረዱ ግበዓቶች የተገኙበት ነው ብለዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክር ላይ የፓርቲዎች ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ በበኩላቸው ፓርቲዎች የወጣቶችን፣ የአካል ጉዳተኞችንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ የበለጠ ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአባልነት መዋጮን በተመለከተም ፓርቲዎች አባላቶቻቸውን ሊያበረታቱ እንደሚገባም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን ስራ ላይ ለማዋል የጀመራቸውን ተግባራት ሊያጠናክር እንደሚገባ ጠቁመው ፓርቲዎችም ይሄንኑ ስራ ሊደግፉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት ይሰራል - አቶ ፍቃዱ ተሰማ
Jul 11, 2025 72
ጎንደር፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ መጪው ምርጫ የትብብርና ፋክክር የዲሞክራሲ ባህል የሚገነባበት እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ። ከተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የተውጣጡ የፓርቲው የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች የተሳተፉበትና በጎንደር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የግምገማ መድረክ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ማምሻውን ተጠናቋል። አቶ ፍቃዱ ተሰማ የግምገማ መድረኩ ማጠቃለያን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ ፓርቲው መጪው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን መላ አባላቱን የማዘጋጀት ስራዎቹን በትኩረት ያከናውናል ብለዋል። ለዚህም የአባላት የስነ-ምግባር ደንቦችን በማዘጋጀት በምርጫው የትብብርና ፉክክር ዴሞክራሲያዊ ባህል እንዲዳብር እንደሚሰራም ተናግረዋል። አባላቱ በፓርቲው እሳቤዎች፣ መተዳደሪያ ደንብና አሰራሮች ዙሪያ ወጥና የተቀራረበ ግንዛቤ በመያዝ ተቋማዊ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲወጡ አቅማቸውን የመገንባት ስራ ይከናወናል ብለዋል። የፓርቲው አደረጃጀቶች በልማት በሠላምና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል እንደሚሰሩም ጠቁመዋል። የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደፓርቲና መንግስት ሰፋ ያሉ ውጤቶች የተመዘገቡበትና የማንሰራራት ዘመን በተጨባጭ የታየበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዓመቱ በፓርቲው ውስጥ የአመለካከት፣ የተግባር አንድነትና ህብረ ብሔራዊነት የተጠናከረበት እንደነበርም ተናግረዋል። ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚደረገው ጥረት በጎ ጅምር የታየበት፣ ኢኮኖሚያዊ እድገቱ የሀገሪቱን በጀት በትሪሊዮን እንዲጸድቅ ያስቻለና የእዳ ቅነሳ የተደረገበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራና የከተሞች ኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤታማ እንደነበርም አብራርተዋል፡፡ በሠላም ማስከበር ሂደቱ የታጠቁ ኃይሎች የመንግስትን የሠላም አማራጭ ተቀብለው ተሃድሶ በመውሰድ በስፋት ወደ ሠላማዊ ህይወት መመለሳቸውንም አስታውሰዋል። በቀጣይም ሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳካ ፓርቲው የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ኃላፊው አረጋግጠዋል።
በበጀት አመቱ በከተማዋ በተከናወኑ ስኬታማ የሰላም ተግባራት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ ነበር - የከተማዋ የምክር ቤት አባላት
Jul 11, 2025 74
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት አመቱ በከተማዋ በተከናወኑ ስኬታማ የሰላም ተግባራት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበር የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። 3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ እና የበጀት አመቱ ማጠቃለያ ስብሰባ እየተካሄደ ነው። በስብሰባው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና አቅጣጫዎችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። በዚሁ ጊዜ በ2017 በጀት ዓመት የከተማዋን ሰላም በማስጠበቅ፣ የነዋሪዎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ እንዲሁም አህጉራዊና ዓለም-አቀፋዊ ሁነቶችን በማስተናገድ ስኬታማ ሥራዎች መሰራታቸውን ነው ያብራሩት። በከተማዋ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በርካታ የጸጥታና የወንጀል ድርጊቶችን በመለየትና አስቀድሞ በመከላከል ብሎም ህጋዊ እርምጃዎችን መውሰድ መቻሉን አንስተዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላትም የከተማዋን ሰላምና ደህንነት ከማረጋገጥ አንጻር የተከናወኑት ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊና የምክር ቤቱ አባል ሊዲያ ግርማ በበጀት ዓመቱ በከተማዋ ሰላም በመረጋገጡ የልማት ስራዎች ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲከናወኑ በትኩረት መሰራቱን ገልጸዋል። የከተማው ነዋሪ ህብረተሰብም በወንጀል መከላከል ሂደትና ሰላም በማስጠበቅ ሂደት ላይ የነበረው ተሳትፎ በየጊዜው እየጎለበተ መምጣቱን እንዲሁ። ሰላም ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ልማት የማይተካ ሚና አለው ያሉት ደግሞ ሌላዋ የምክር ቤት አባል ወርቅነሽ ምትኩ (ዶ/ር) ናቸው።   በከተማዋ ለተመዘገቡ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጦች የሰላምና ጸጥታ መረጋገጥ ትልቅ ሚና መጫወቱንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ ሌላው የምክር ቤት አባል ኢቲሳ ደሜ(ዶ/ር) ህዝብን ያሳተፈ የሰላምና ልማት ሥራ የተሻለ ውጤት እንደሚያመጣ አዲስ አበባ ማሳያ ናት ብለዋል።   ከተማዋ የአህጉራዊና አለም አቀፋዊ ተቋማት መቀመጫና የአፍሪካ መዲና በመሆኗ ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ በኩል ህብረተሰቡ ቀጣይነት ያለው ድጋፉንና ተሳትፎውን ማስቀጠል እንደሚገባ በመጥቀስ። በከተማዋ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንዲረጋገጡ የምክር ቤቱ አባላት ድጋፍና ክትትላቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። የከተማዋን ሰላም በማስቀጠል ሂደትም ነዋሪው ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥል የምክር ቤት አባላቱ ጥሪ አቅርበዋል።
በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ በውጤታማነት ተጠናክሮ ቀጥሏል - ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)
Jul 11, 2025 89
አርባምንጭ ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ) ፡-በሀገሪቱ በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ በውጤታማነት ተጠናክሮ መቀጠሉን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ተናገሩ ። የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተገመገመ ነው። የብልጽግና ፓርቲ ዓለም አቀፍና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ በኢኮኖሚው በፖለቲካውና፣ በዲፕሎማሲው ዘርፍ በዓለም አደባባይ ፈጣን ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች ብለዋል። ይህን ለማሳካትም የተረጋጋ የፖለቲካ ምህዳር በመፍጠር በህዝቦች መካከል ወንድማማችነትና እህትማማችነት እየተጠናከረ የመጣበት ዓመት ነው ሲሉም ገልጸዋል።   የሀገርን እድገት ወደ ኋላ ለመመለስ የሚጥሩ አካላት በህዝብና በመንግስት ትብብር ሴራቸው እየከሸፈ መምጣቱንም ገልጸዋል። በህብረብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ትርክት ግንባታ ሂደትም ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ያነሱት ቢቂላ (ዶ/ር) ''እስካሁን የተመዘገበውን ስኬት ለማስቀጠል አበክረን እንሠራለን'' ብለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው ፓርቲው የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል።   የብሔር ብሔረሰቦችን መብት በማስከበር የተረጋጋች ሀገር የመገንባት ሂደቱም በተሻለ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። በቀጣይም የተጀመሩ ልማቶችን በማስቀጠል የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ጠቁመዋል። ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው መድረክ ከሁሉም ክልሎች የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤታማ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገሩ ተግባር ይጠናከራል
Jul 10, 2025 116
  ሐረር፤ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)፡-በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤታማ ስራዎች ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ በሐረር ከተማ ለሁለት ቀናት ሲያካሂደው የቆየው የ2017 እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 እቅድ ተግባቦት መድረክ ዛሬ ተጠናቋል። በመድረኩ የፌደራልና የክልል የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ አመራሮች እንዲሁም የፓርቲው የወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ተሳትፈዋል። በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለስ ዓለሙ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ በ2017 በጀት ዓመት የዴሞክራሲ ባህል እሴትን ለማጠናከር የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።   የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር ከመስራት አንጻር በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በጋራ ምክር ቤቶች በመደራጀት አብሮ የመስራት ባህል እየዳበረ መምጣቱን ጠቅሰዋል። ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የተጀመሩ ስራዎች አዲስ ባህልና ልምድ እያመጡ ስለመሆኑም አንስተዋል። የጋራ ስራዎቹ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በቁርጠኝነት መስራታቸውን አጎልብተው እንዲቀጥሉም አመልክተዋል። በአሁኑ ወቅት በየደረጃው ያለው የመንግስት አካላትና ሲቪል ማህበረሰብ በጋራና በቅንጅት የሚሰሩበት ጅምር ሁኔታ መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በተለይ የወጣቶችና ሴቶች አስተዋጽኦን ለማላቅና ተሳትፏቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ብሎም ተጠቃሚነታቸውን ለማጎልበት መድረኩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አንስተዋል።   በቀጣይም ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሰረት ትኩረት ተሰጥቶ እና ባህል አድርጎ እንደሚሰራም አመላክተዋል።
የከተማው ነዋሪዎች ሰላምን ለማፅናት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Jul 10, 2025 111
ደብረብርሃን ፤ ሐምሌ 3/ 2017 (ኢዜአ)፡- የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር በአካባቢው ሰላምን ለማፅናት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንደገለጹት፤ የጸጥታ ሃይሉ ከሕብረተሰቡ ጋር በመተባበር ሰላም እንዲከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።   በዚህም በከተማዋ የሚካሄዱ የኢንዱስትሪ፣ የኢንቨስትመንትና የንግድ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቅሰዋል። ይህም ስራ እድል እንዲስፋፋ፣ የገቢና ሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ እንዲሆኑ ምቹ መደላድል መፍጠሩን ገልጸዋል። በከተማዋ አሁን ላይ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተካሄዱ እንደሚገኙ አስረድተዋል። የልማት ሁሉ መሰረት የሆነውን ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ሁሉ ሕብረተሰቡ ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የተለመደ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላልፈዋል። የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብሩ ዓላማም የከተማው ነዋሪዎች ከጸጥታ ሃይሉ ጎን በመሰለፍ የህግ ማስከበር ስራው ይበልጥ በውጤታማነት በማስቀጠሉ ሂደት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ለማበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።   ከህግ አስከባሪዎች መካከል ሀምሳ አለቃ ሰይፈ ደምሰው በሰጡት አስተያየት፤ ሰላምን አፅንቶ በማስቀጠል ለልማት የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ይበልጥ ለማጠናከር ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀናጅተወ በትኩረት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ሌላው የመርሃ ግብሩ ተሳታፊ ፈለቀ በየነ በበኩላቸው፤ የአካባቢውን ሰላም በማፅናት የልማት ስራዎቻቸው ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጎዳና ላይ ትርኢቶችና ሌሎች ዝግጅቶች ተካሂደዋል።
በብሔረሰብ አስተዳደሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል
Jul 10, 2025 95
ሰቆጣ ፤ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት መከናወናቸውን የብሔረሰብ አስተዳደሩ አስታወቀ። የብሔረሰብ አስተዳደሩ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምን የሚገመግምና የቀጣይ 90 ቀናት ዕቅድ ማስተዋወቂያ መድረክ በሰቆጣ ከተማ እየተካሄደ ነው። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሃይሉ ግርማይ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላምና ፀጥታ ተግባር በመካሄዱ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል።   በልማት ሥራም ለመልካም አስተዳደር ምክንያት ሆኖ የቆየው የሰቆጣ አዳሪ ትምህርት ቤትን ጨምሮ የስርዓተ ምግብን ለማሻሻል በዓመት ከ360 ሺህ በላይ ጫጩት ማስፈልፈያ ማዕከል ግንባታ ስራን ማከናወን እንደተቻለ ገልጸዋል። በተጨማሪም የመስኖ መሰረተ ልማትን በማስፋፋት የግብርና ምርታማነት እንዲያድግ መሰራቱን ጠቁመው፣ የመኽር እርሻ ምርታማነትን ለማሳደግም በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። በፌደራል፣ በክልልና በወረዳ በጀት እየተገነቡ ያሉ መሰረተ ልማቶች በተቀመጠላቸው ጊዜ በጥራት ተገንብተው እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትሉ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የአመራሩን የማስፈፀም አቅም ይበልጥ በማሳደግ በበጀት ዓመቱ የተገኙ ስኬቶችን በአዲሱ በጀት ዓመትም ለመድገም ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አቶ ሃይሉ አስረድተዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ጭምር ያልተቋረጠ የጤና አገልግሎት መስጠት መቻሉን የተናገሩት ደግሞ የብሔረሰብ አስተዳደሩ ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ ናቸው።   በበጀት ዓመቱ በስርዓተ ምግብ ማሻሻል እንዲሁም የወባ እና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን በመከላከልና በማከም በተሰራው ስራም የከፋ ችግር ሳይደርስ ማለፉንም ተናግረዋል። የእናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከልን ጨምሮ 42 የጤና ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆናቸውን የተናገሩት አቶ አሰፋ፤ በጤና ተቋማቱ ዜጎችን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል። የብሄረሰብ አስተዳደሩ የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ በበኩላቸው "በብሔረሰብ አስተዳደሩ በመስኖ ከለማው መሬት ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል ብለዋል። ይህም የአካባቢውን ገበያ ለማረጋጋት ማገዙን ተናግረዋል።   በበጋው ወቅት በ369 ተፋሰሶች ላይ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ መካሄዱን ጠቁመው፣ የለሙትን ተፋሰሶች በስነ እፅዋት ዘዴ ለማጠናከርም ችግኞች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ የክልል፣ የብሔረሰብ አስተዳደሩና የወረዳ አመራሮች ተሳትፈዋል።
የኢትዮጵያና ዛምቢያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በተለያዩ መስኮች ተጠናክሮ ቀጥሏል - አምባሳደር ሮዝ ሳካላ
Jul 10, 2025 122
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እና በዛምቢያ መካከል ያለው ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ግንኙነት በተለያዩ መስኮች ተጠናክሮ መቀጠሉን በኢትዮጵያ የዛምቢያ አምባሳደር ሮዝ ሳካላ ገለጹ። በኢትዮጵያ የዛምቢያ አምባሳደር ሮዝ ሳካላ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ እና ዛምቢያ ዘላቂ እና ዘርፈ-ብዙ ግንኙነት እንዳላቸው ገለጸዋል። ይህም ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እና በተለያዩ ዘርፎችም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። በተለይም ዛምቢያ ኤምባሲዋን በኢትዮጵያ ከከፈተችበት ጊዜ አንስቶ የሁለቱ አገሮች አጋርነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ ከመምጣቱም በላይ የተለያዩ የትብብር ስራዎችም እየተጠናከረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እ.አ.አ በ2017 ሁለቱ ሀገራት የጋራ ኮሚሽን ማቋቋማቸውን ገልጸው፤ ይህም ተጨባጭ ጥቅሞችን ማስገኘቱን ጠቁመዋል። ሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ አቅም እንዳላቸው ገልጸው፤ ከሁለቱም ወገኖች የተውጣጡ የንግድ ባለሙያዎችን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማሰባሰብ ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማሳደግ ጥረት መደረጉን አንስተዋል። የጋራ ኮሚሽኑ በንግድና ኢንቨስትመንት በተለይም በግብርናና በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትስስር እንደሚያጠናክር ጠቁመዋል። ዛምቢያ የአፍሪካን አንድነት ለማጎልበት እና አህጉራዊ አጀንዳዎችን ለማራመድ በተለያዩ መድረኮች በማደራጀት እና በመሳተፍ ንቁ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑን ተናግረዋል ። አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ ቋሚ ውክልና አለማግኘቷ ኢ-ፍትሃዊ ነው ብለዋል። ዛምቢያ ለቀጣናው ኢኮኖሚያዊ ውህደት ትልቅ አስተዋፅዖ እንዳደረገች ገልፀው፤ ፓን አፍሪካኒዝም እንደ መሰረታዊ መርህ እና ከእነዚህ ጥረቶች ጀርባ አንቀሳቃሽ ሃይል ሆኖ ያገለግላል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ለአፍሪካ በርካታ እድሎችን የሚሰጥ ወርቃማ አጀንዳ መሆኑን ገልጸው፤ በትብብር መተግበር እንደሚገባ አሳስበዋል።
ማህበራዊ
ኢጋድ የሴቶች የመሬት ባለቤትነትና ውሳኔ ሰጪነት ሚና ለማሳደግ የሚደረጉ ጥረቶችን እንደሚደግፍ ገለጸ
Jul 12, 2025 13
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ሴቶች የመሬት ባለቤትነት መብታቸው እንዲከበር እና በአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎች ላይ የመሪነት ሚናቸው እንዲያድግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታወቀ። ኢጋድ ከሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም አንስቶ በኬንያ ናይሮቢ ስርዓተ ጾታ፣ መሬት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ግንባታ ላይ ሲያካሂድ የቆየው ቀጣናዊ ምክክር ዛሬ ተጠናቋል። በምክክሩ ላይ ሴት የፓርላማ አባላት፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት ተወካዮች፣ የቴክኒክ ባለሙያዎች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ሁነቱ የስርዓተ ጾታ እኩልነት፣ የመሬት አስተዳደር እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ግንባታ ላይ የሚሰሩ ተቋማትን በአንድ መድረክ ያገናኘ ነው። ውይይቱ የመሬት መብቶችን ማስጠበቅ እና ሴቶችን ያሳተፈ የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ላይ ሁሉን አቀፍ የፖሊሲ ምክክር ማድረግ እና ቀጣናዊ ትብብርን የማጠናከር ውጥን ያነገበ ነው።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ምክትል ዋና ፀሐፊ መሐመድ አብዲ ዋሬ ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር ምክክሩ ሴቶች በመሬት ባለቤትነት እና በአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችል ጠንካራ አቋም የተያዘበት መሆኑን አመልክተዋል። በቀጣናው የሚገኙ ሴቶች ለመሬት ልማት፣ ግብርና እና ለዜጎች ደህነት መጠበቅ ወሳኝ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ቢገኝም በመሬት ባለቤትነት እና ውሳኔ ሰጪነት ላይ ፈተናዎች እያጋጠሟቸው ነው ብለዋል። ሴቶችን ማብቃት ለፍትህ፣ እኩልነት እና ዘላቂ ልማት መረጋገጥ ቁልፍ እንደሆነ ተናግረዋል። የሴት ፓርላማ አባላት ቀጣናዊ ማዕቀፍ እና ቀጣናዊ የፖሊሲ ሰነድ ዝግጅት የውይይቱ ቁልፍ ውጤቶች ናቸው ብለዋል። የአሰራር ማዕቀፎቹ በመሬት መብቶች እና በማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ላይ ተግባራዊ ምላሽ መስጠት የሚያስችሉ እና የፖለቲካ ቁርጠኝነት የታየባቸው እንደሆነ አብራርተዋል። ሀገራት ቀጣናዊ ማዕቀፎቹን የብሄራዊ እቅዶቻቸው ጋር አጣጥመው እንዲተገብሩና ከቀጣናዊ የአሰራር ስርዓቶች ጋር ስራቸውን እንዲያስተሳስሩ ጥሪ አቅርበዋል። የፓርላማ አባላቱ የለውጥ መሐንዲሶች ናቸው ያሉት ምክትል ዋና ፀሐፊው ሴቶች የመሬት ባለቤት እንዲሆኑና በአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ የመሪነት ሚና እንዲኖራቸው አበክረው እንዲሰሩ ጠይቀዋል። ኢጋድ የሴቶችን የመሬት ባለቤትነት ለማረጋገጥ እና በማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ያላቸውን ሚና ለማሳደግ ቁርጠኛ እንደሆነ መግለጻቸውን ተቋሙ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ቀጣናዊ ምክክር ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳንና ዩጋንዳ የተካሄዱ ምክክሮች ማጠቃለያ ነው።
በክልሉ የሚያጋጥሙ በሽታዎችን ፈጥኖ በመለየት ምላሽ መስጠት የሚያስችል የጤና ስርዓት የመዘርጋት ስራ ይጠናከራል
Jul 11, 2025 62
ባህርዳር፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በየጊዜው የሚያጋጥሙ በሽታዎችን ፈጥኖ በመለየት ምላሽ መስጠት የሚያስችል የጤና ስርዓት የመዘርጋት ስራ እንደሚጠናከር በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) ገለጹ። በአማራ ክልል ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚተገበር "የጤና ደህንነት ትግበራ /health security activity/" የተሰኘና የህብረተሰቡን ጤንነት የሚያስጠብቅና የሚያሻሽል ፕሮጀክት ዛሬ በባህር ዳር ከተማ ይፋ ተደርጓል።   በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ፣ የክልሉ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የጤና ስርዓቱን ለማሻሻል የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ ነው። በዛሬው እለት ይፋ የተደረገው ፕሮጀክትም በክልሉ በየጊዜው የሚያጋጥሙ የጤና ችግሮችን ለይቶ መፍታት የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል። ፕሮጀክቱ የበሽታ ቅኝት በማድረግ፣ በፍጥነት በመለየትና ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ አፋጣኝ መፍትሄ ለመስጠት አጋዥ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ የታለመለትን ግብ እንዲመታ የክልሉ መንግስትና ህዝብ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ያደርጋሉ ብለዋል።   የአማራ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በላይ በዛብህ፤ ፕሮጀክቱ በክልሉ በተመረጡ 56 ወረዳዎች የሚተገበር ነው ብለዋል። በክልሉ በጤናው ዘርፍ የሚታዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የቤተ ሙከራ አቅምን ማሳደግና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ማጎልበት ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል።   "የጤና ደህንነት ትግበራ /health security activity/" ፕሮጀክት ምክትል ኃላፊ ዶክተር ኤልያስ ዋለልኝ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ የአማራ ክልልን ጨምሮ በአፋርና በትግራይ ክልሎች የሚተገበር መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም ፕሮጀክቱ ከሰው ወደ ሰው፣ ከእንስሳት ወደ ሰው፣ ከሰው ወደ እንስሳትና ከአካባቢ ወደ ሰው የሚተላለፉ በሽታዎችን አስቀድሞ በሚካሄድ ቅኝት በመለየት ለመከላከል አልሞ የሚሰራ ነው ብለዋል። በመድረኩ የክልልና የፌደራል የጤናው ዘርፍ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በጌዴኦ ዞን የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በትብብር እየተሰራ ነው - የዞኑ አስተዳደር
Jul 11, 2025 68
ዲላ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከህብረተሰቡ እና ከአጋር አካላት ጋር በትብብር የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። በዞኑ ዲላ ከተማ አስተዳደር በ40 ሚሊዮን ብር ወጪ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ እየተከናወነ ነው።   ግንባታው የዞኑ አስተዳደር ከዓለም አቀፉ የትምህርትና ባህል ተራድኦ ድርጅት(WECA) ጋር በመተባበር የሚከናወን ሲሆን ግንባታውን በተያዘው ዓመት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረግ ተመላክቷል። የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በዞኑ የትምህርት ስብራትን በዘላቂነት ለመቅረፍና ጥራትን ለማስጠበቅ ከህብረተሰቡ እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር እየተሰራ ነው።   በተለይ በተያዘው በጀት ዓመት በዞኑ 80 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ያሉባቸውን የመሰረተ ልማት ችግር በማሻሻል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትኩረት እንደሚደረግ ገልጸዋል። የትምህርት ቤቱ ግንባታ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ ክትትል የሚደረግ መሆኑን አንስተው የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ሞዴል ትምህርት ቤት ከመፍጠር ባለፈ ደረጃውን ወደ አዳሪ ትምህርት ቤት ለማሳደግ መታቀዱንም ገልጸዋል።   ትምህርት ቤት የእውቀት መገበያያ ብቻ ሳይሆን የትውልዱ የስብዕና ግንባታ ማዕከል መሆኑን ያነሱት ደግሞ የዓለም አቀፉ የትምህርትና ባህል ተራድኦ ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ባንግ ቱንጋዋን ናቸው። ድርጅታቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የትምህርት መሰረተ ልማትን በማስፋፋት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ነው ብለዋል። በዲላ ከተማ ከዞኑ አስተዳደር ጋር በመተባበር የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከመገንባት ባሻገር በትምህርት ቤቱ የውጭ ቋንቋዎችን በማስተማር የትምህርት ስርዓቱን እየደገፈ መሆኑን ጠቁመዋል።   የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዘማች ክፍሌ በበኩላቸው የትምህርት ቤቱን የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በተያዘው ዓመት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረግ ተናግረዋል። ይህም 13 መማሪያ ክፍሎችን ጨምሮ የአስተዳደርና የመጸዳጃ ህንጻዎችን እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ያካተተ ሲሆን ለዚህም ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅትም አራት የመጀመሪያ ደረጃ የመማሪያ ክፍሎች ግንባታ መጠናቀቃቸውን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ በስደተኞች አያያዝ አርዓያነት ያለው ተግባር እያከናወነች ነው
Jul 11, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በስደተኞች አያያዝ አርዓያነት ያለውና የሚደነቅ ተግባር እያከናወነች ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ረዳት ተጠሪ ዴቪድ ካርፕ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከሃያ ስድስት አገራት በተለያየ ምክንያት የመጡ ከ1 ሚሊዮን በላይ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን በመቀበል ተገቢውን ጥበቃና ከለላ እየሰጠች ትገኛለች። በኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ረዳት ተጠሪ ዴቪድ ካርፕ፥ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የስደተኞች አያያዝ መርህን ባከበረ መልኩ ለስደተኞች አገልግሎት እየሰጠች እንደምትገኝ ለኢዜአ ገልጸዋል። ስደተኞች ባሉባቸው አካባቢዎች የመንገድ፣ የውሃ፣ የመብራት፣ የትምህርት፣ የጤና እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ተገንብተው አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ስደተኞች ከተቀባዩ የህብረተሰብ ክፍል ጋር በማስተሳሰር በስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑንም እንዲሁ፡፡ ይህም ኢትዮጵያን ለስደተኞች ከፍተኛ ትኩረት ከሚያደርጉ እና ክብር ከሚሰጡ የዓለም ሀገራት መካከል አንዷ እንደሚያደርጋት አንስተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በስደተኞች አያያዝ ዙሪያ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለሌሎች የዓለም አገራት አርዓያ እንደሚሆኑም ጠቁመዋል፡፡ ረዳት ተጠሪው አክለውም የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ለዚህ ተግባራቸው ምስጋና ይገባቸዋል ነው ያሉት፡፡ በቀጣይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን በስደተኞች አያያዝ ላይ ያለውን ቅንጅታዊ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡  
ኢኮኖሚ
በአርባምንጭ ከተማ እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የብልጽግና ጉዞ ስኬት ማሳያ ናቸው - ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር)
Jul 11, 2025 62
አርባምንጭ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በአርባምንጭ ከተማ እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶች የብልጽግና ጉዞ ስኬት ማሳያ ናቸው ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና አለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ገለጹ። የፌደራልና የክልሎች የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊዎች ማምሻውን የአርባምንጭ ከተማ ዓለም አቀፍ ስታዲየምና የከተማዋን የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴዎች ጎብኝተዋል። ከጉብኝት በኋላ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት በአርባምንጭ ከተማ እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የብልጽግና ጉዞ ስኬታማነት ማሳያ ናቸው።   በአምስት ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ስታዲየም ከሀገር አልፎ በአህጉር ደረጃ ትልቅ ፋይዳ ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ስታዲየሙ የአትሌቲክስ መሮጫና 25 ሺህ ሰው የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን የተለያዩ ጨዋታዎችን ማስተናገድ የሚችል ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን መመልከታቸውን ተናግረዋል። አክለውም በህብረተሰብ ተሳትፎና በመንግስት ትብብር እየተገነባ ያለው ስታዲየም የሀገሪቱን የእግር ኳስ ዕድገት ከፍ እንደሚያደርግ ያላቸውን እምነት ገለጸዋል። በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማትም በፓርቲው እሳቤ መሠረት ከተሞችን ጽዱና ውብ እንዲሁም ለህዝብ ምቹ የማድረግ ትልም መገለጫ ሆኖ ማግኘታቸውን ጠቁመዋል። የኮሪደር ልማቱ ለአርባምንጭ ከተማ ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ በመሆን ዘርፉን በማነቃቃት ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ ፋይዳ ያለው ነው ብለዋል።   ብልጽግና ፓርቲ በሁሉም የልማት መስኮች የህዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአርባምንጭ ከተማ መካሄዱ ይታወቃል።
ጠንካራ የሚዲያ ተቋም በመገንባት የልማት ስኬቶችን በቅንጅት ለህዝብ ማድረስ ይገባል
Jul 11, 2025 62
አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 4/2017 (ኢዜአ)፡-ጠንካራ የሚዲያ ተቋም በመገንባት የልማት ስኬቶችን በቅንጅት ለህዝብ ማድረስ እንደሚገባ የብልጽግና ፓርቲ ዓለም አቀፍና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) አስታወቁ። የብልጽግና ፓርቲ ዋናው ጽህፈት ቤት የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ግምገማ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሄዷል።   በመድረኩ ላይ ኃላፊው እንዳሉት፤ ጠንካራ የሚዲያ ተቋም በመገንባት በፓርቲው የተመዘገቡ የልማት ድሎችን ለህዝብ ለማድረስ በቅንጅት ይሰራል። ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክር ሚዲያ በመፍጠር የተገኙ የልማት ድሎችን ለህዝብ ማድረስ ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ተዓማኒነት ባለው ተግባቦት የህዝቡን አንድነት ለማላላት የሚጥሩ ጽንፈኞች ሙከራን እንዲከሽፉ መደረጉን ተናግረዋል። በሀገሪቱ የተመዘገቡ አስደናቂ የልማት ውጤቶችን ለህዝብ ተደራሽ በማድረግ በኩል ያሉ ውስንነቶችን በመቅረፍ ጽንፈኛ ኃይሎች የሚያካሄዱትን አሉታዊ እንቅስቃሴ አስቀድሞ ለመመከት ከመቼውም ግዜ በላይ መስራት ይገባል ብለዋል። በፓርቲው የተመዘገቡ የልማት ድሎችን ከማሳወቅ አንፃር ማህበራዊ ሚዲያን በማጠናከር ተገቢውን ሽፋን እንዲያገኙ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።   የብልጽግና ፓርቲ በሁሉም መመዘኛዎች የህዝብን አደራ ተቀብሎ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ ነው ያሉት ቢቂላ (ዶ/ር) ፓርቲው ከጽንፈኝነት ይልቅ ህብረ-ብሔራዊ ኢትዮጵያዊነትን የሚያቀነቅን እንደሆነም አክለዋል። ''ጽንፈኞች የትርክትና የአጀንዳ የበላይነት የላቸውም'' ያሉት ኃላፊው ግልጽ ፕሮግራም፣ አስተሳሰብና እሳቤ ያለው ብልጽግና ፓርቲ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተግቶ እየሠራ መሆኑን አስረድተዋል። ሁሉም ክልሎች የሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም በፓርቲው የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ህዝብ ይበልጥ ሊያደርሱ እንደሚገባም ኃላፊው አመልክተዋል። የብልጽግና ፓርቲ ዋናው ጽህፈት ቤት የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ግምገማ የተጠናቀቀ ሲሆን የመድረኩ ተሳታፊዎችም በነገው ዕለትም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ያከናውናሉ።
የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶች በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ እንዲገበያዩ መደረጉ የሪፎርም ስራዎችን የበለጠ ያጠናክራል - ሚኒስትር አህመድ ሽዴ
Jul 11, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶች በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ እንዲመዘገቡና እንዲገበያዩ መደረጉ የሪፎርም ስራዎችን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ። የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶችንና ሌሎች የሰነደ ሙዓለ ንዋዮችን የማገበያየት ሂደት በይፋ ጀምሯል።   በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ እንደተናገሩት ገበያው መጀመሩ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶችን በሰነደ መዋለ ነዋዮች አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ ለህዝብ ማቅረብ የሚያስችል ነው። አጠቃላይ የመንግስትን ፋይናንስ አስተዳደር የማዘመን ሪፎርምን ለማሳካት ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶች የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያዎች እንዲመዘገቡና እንዲገበያዩ መደረጉ የሪፎርም ስራዎችን የበለጠ ለማጠናከር ይረዳል ብለዋል። የተጠናቀቀው በጀት አመት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እያከናወነች ያለው የሪፎርም ስራ በስኬት የተጠናቀቀበት እንደሆነ በመግለጽ በቀጣይ በጀት አመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ጨረታዎች በገበያ መርሆች እንዲመሩ መደረጉን ተከትሎ የታዩት ለውጦች አበረታችና ውጤታማ ናቸው። እነዚህ ማሻሻያዎች የበጀት ጉድለትን ለመሙላት ከሚደረገው ጥረት በላይ ፋይዳ ያላቸው ሲሆኑ በኢኮኖሚው እንዲሁም በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ላይ ተአማኒነትና ተገማችነትን ለማስፋት የሚረዱ ናቸው።   የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ በበኩላቸው መንግስት ያጋጠሙ የምጣኔ ሃብት ችግሮችን በመፍታት የተረጋጋና ዘላቂ እድገት ማምጣት የሚያስችል ማሻሻያ ቀርጾ እየተገበረ መሆኑን አንስተዋል። ከእነዚህ መካከል ግልጽና ተአማኒነት ያለው የካፒታል ገበያ መገንባት አንዱ ሲሆን የዋጋ መረጋጋትን ለማምጣት፣ የገንዘብ ፖሊሲ መሳሪያዎች ውጤታማነትን ለማሳደግ ይረዳል ብለዋል። በተመሳሳይ ቁጠባና ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት፣ ከውጭ እዳ ጫና ጋር የሚገጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ ገበያው ትልቅ ሚና ይጫወታል ነው ያሉት።   የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃና ተኸልኩ የገበያው መጀመር ኢትዮጵያ በሀገር በቀል ምጣኔ ሃብት ማሻሻያው እያከናወነች ባለው ሁሉን አቀፍ ጠንካራና ገበያ መር ምጣኔ ሃብት ግንባታ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ገልጸዋል። ኢንቨስተሮች በገበያው ላይ በንቃት መሳተፍ የሚችሉበትን እድል የፈጠረና የመንግስት የእዳ አስተዳደር የማዘመን ሂደት ላይም ትልቅ አስተዋጽኦ የሚኖረው እርምጃ እንደሆነ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሰነደ ሙዓለ ነዋዮች የገበያ መድረክ ሲሆን በመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት የተቋቋመ ነው። የገበያው ዋና ዓላማ ውጤታማ የካፒታል ማሰባሰብ ስራዎችን በማጠናከር የኢትዮጵያን ምጣኔ ሃብት እድገት ግልጽና ደህንነቱ በተጠበቀ የካፒታል ገበያ ስራዎች መደገፍ ነው።    
በመዲናዋ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን 219 በማድረስ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ ተደርጓል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 11, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦በ2017 በጀት ዓመት በመዲናዋ የገበያውን ሁኔታ ለማረጋጋት የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎችን 219 በማድረስ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች በቀጥታ እንዲደርስ መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። 3ኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ እና የበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ ስብሰባ የመጀመሪያ ቀን ውሎ ተካሂዷል። በስብሰባው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና አቅጣጫዎች ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።   በከተማዋ ሰላምና ጸጥታ፣ በተቋማት ሪፎርም፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በመሰረተ ልማትና በማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች የተከናወኑ ተግባራትን ዝርዝር ሪፖርት አቅርበዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት በበጀት ዓመቱ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል አቅም በተቋማት መፈጠሩን አንስተዋል። 347 አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በመከላከል በተቋማት ውስጥ ግልጽነት እንዲፈጠርና የተገልጋይ እንግልት እንዲቀንስ መደረጉን ገልጸዋል። ይሁንና በአንዳንድ ተቋማት አሁንም ቢሆን በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች በመኖራቸው የማስተካከያ እርምጃ በመወሰድ ላይ ነው ብለዋል። በበጀት ዓመቱ በሌብነትና ብልሹ አሰራር የተሳተፉ አመራርና ሠራተኞች ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸው፥ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የትምህርት ቤቶችንና የጤና ተቋማትን ደረጃ በማሻሻልና አዳዲስ በመገንባት እንዲሁም የምገባ ማዕከላትን በማስፋት ትውልድ ላይ ውጤታማ ስራዎች መሰራቱንም ከንቲባዋ አብራርተዋል። በበጀት ዓመቱ በከተማ ግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች ለ336 ሺህ የከተማዋ ሥራ ፈላጊዎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ከንቲባዋ አንስተዋል። በበጀት ዓመቱ ከተማዋን ከጎበኙ አንድ ሚሊዮን የውጭ ቱሪስቶች 143 ቢሊዮን ብር በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ወደ ኢኮኖሚው ፈሰስ መደረጉን አመልክተዋል። በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን 9 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሀገር ወስጥ ጎብኚዎች ተዘዋውረው እንደጎበኟቸው እና በርካታ ገቢ እንዳስገኙም አንስተዋል። በሌላ በኩል የገበያውን ሁኔታ ለማረጋጋትና የኑሮ ወድነቱን ለማቃለል ከተማ አስተዳደሩ ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ለተለያዩ ዘርፎች በመመደብ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረጉን ነው የገለጹት። አዳዲስ የገበያ ማዕከላትን በማስፋፋት እና የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎችን 219 በማድረስ አምራቾች በቀጥታ ምርቶቻቸውን ለነዋሪዎች በተመጣጠኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚህም የገበያ ሰንሰለቱን በማሳጠር አምራቹንም ሸማቹንም ተጠቃሚ አድርገናል ነው ያሉት። በትራንስፖርት፣ በጤና መድህን፣ በዳቦ ምርትና በምገባ አቅርቦትን በመጨመር የኑሮ ጫናውን የሚያቃልሉ ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። የገቢ አሰባሰብን በማሳደግ እና ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድም በበጀት ዓመቱ ስኬት መመዝገቡን ከንቲባዋ ተናግረዋል። በከተማ አስተዳደሩ፣ በባለሃብቱ እና በህብረተሰብ ተሳትፎ በርካታ የልማት ሥራዎችና የስፖርት ማዘወተሪያና የህጻናት መጫወቻ ስፍራዎች መሰራታቸውን አስገንዝበዋል። ከተማ አስተዳደሩ የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን በማስቀጠል በአዲሱ በጀት ዓመት በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።          
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች ለሀገር እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መደላድል ይፈጥራል - ቋሚ ኮሚቴው
Jul 11, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ያላቸውን ሚና በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መደላድል እንደሚፈጥር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። ቋሚ ኮሚቴው የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት የባለድርሻ አካላት አስረጂ መድረክ አካሂዷል።   የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ቤተልሔም ላቀው(ዶ/ር) ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ በቋሚ ኮሜቴው የተዘጋጁ ጥያቄዎችን በዝርዝር አቅርበዋል። በረቂቅ አዋጁ የተካተቱ አንቀጾች ላይ የሚስተዋሉ የግልጽነትና የትርጓሜ ለውጥ የሚያመጡ ሃሳቦች በድጋሚ ሊፈተሹ እንደሚገባ አንስተዋል። እንዲሁም የረቂቅ አዋጁን የህግ ማዕቀፍ ዝግጅት፣ የአጋር አካላት ሚና እና የአዋጁን አስፈላጊነት በሚመለከት ማብራሪያ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር)፤ ከቋሚ ኮሚቴው ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በምላሻቸውም ረቂቅ አዋጁ እንደሀገር የሃብት ምንጭ የሆኑ አዳዲስ አማራጮችንና አሰራሮችን ለማስፋት ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል። በዋናነት መንግስት የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለውን ተግባር ''ከሃሳብ እስከ አምራችነት'' የሚለውን እሳቤ የሚደግፍ መሆኑንም አንስተዋል። ረቂቅ አዋጁ የወጣቱን አምራችነት ለማሳደግ እንዲያግዝ ታልሞ በጥንቃቄ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመው፥ ለዚህም አስቻይ የሆኑ የህግ ማዕቀፎችን ለማካተት ጥረት ተደርጓል ነው ያሉት። ቋሚ ኮሚቴው ረቂቅ አዋጁን በሚመለከት የሰጠው ግብረ መልስ ጉድለቶችን ለማረምና ለመፈተሽ የሚያግዝ በመሆኑ የቀጣይ የቤት ስራ በማድረግ የመፈተሽ ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ረቂቅ አዋጁ ሀገሪቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላትን የማምረት አቅም ለማጉላት እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በተጨማሪም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያለው አበርክቶ የጎላ መሆኑን ገልጸው፤ በእውቀትና ፈጠራ የተመሰረተ ኢኮኖሚ ለመገንባት አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥር ጠቁመዋል። ረቂቅ አዋጁን ይበልጥ ለማዳበር ስታርታፖችንና ባለድርሻ አካላትን በቅርበት የማወያየትና ግብዓት የማሰባሰብ ስራ መከናወኑን ጠቁመዋል።   በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በሰጡት ማጠቃለያ፤ የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ለአካታች ኢኮኖሚ ግንባታ አስቻይ ሁኔታን እንደሚፈጥር አብራርተዋል። ረቂቅ አዋጁ ኢትዮጵያ ያላትን የወጣት ኃይል በተገቢው መልኩ ለመጠቀምና የፈጠራ ሃሳብ ጥቅም ላይ እንዲውል ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። የተለያየ የፈጠራ ሃሳብ፣ ችሎታና በቴክኖሎጂ የዳበረ እውቀት ያላቸው ስታርታፖች በመረጡት መስክ ተሰማርተው ከሀገር አልፎ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አዋጁ አዎንታዊ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል። የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅ ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ያላቸውን ሚና በማሳደግ ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑንም ገልጸዋል።
በዞኑ በዲጂታላይዜሽን የታገዘ አገልግሎት ለማህበረሰቡ በመስጠት የተገልጋይን እርካታ ለማረጋገጥ ትኩረት ተደርጓል
Jul 10, 2025 99
ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦በሰሜን ሸዋ ዞን በዲጂታላይዜሽን የታገዘ ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት ለማህበረሰቡ በመስጠት የተገልጋይን እርካታ ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። የሰሜን ሸዋ ዞን የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ በከተሞች የኮሪደር ልማትና በዲጂታላይዜሽን አተገባበር ላይ ዛሬ ከባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል። የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በውይይቱ ላይ እንደገለጹት በከተሞች ተአማኒነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ዲጂታላይዜሽን የአሰራር ሥርአት እየተዘረጋ ነው።   የዲጂታል አሰራሩ በየደረጃው ያሉ የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች ለተገልጋዩ ማህበረሰብ ግልጽና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ ባለፈ ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ያግዛል ብለዋል። በአዲሱ በጀት ዓመት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የተገልጋይን እርካታ ለመፍጠር ከሚሰራው ሥራ በተጨማሪ በከተሞችና በገጠር አካባቢዎች የኮሪደር ልማትን በማስጀመር የህብረተሰቡን አኗኗር ለማዘመን ትኩረት እንደሚሰጥም አስገንዝበዋል። የዞኑ ከተሞችና የገጠር አካባቢዎች ለማዘመን በሚሰራው ሥራም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አስተዳዳሪው አሳስበዋል። በዞኑ የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ብርቃብርቅ ተሾመ በበኩላቸው እንዳሉት ከተሞችን ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ ነው።   ለዚህም በዞኑ ሥር ባለችው የሸዋ ሮቢት ከተማ የኮሪደር ልማት ግንባታ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ተጀምሮ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ቡልጋ፣ አረርቲና ለሚ ከተሞችን ጨምሮ በዞኑ ሥር ባሉ ዘጠኝ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራን ለማስጀመር የሚያስችል የጥናት ሥራ ተጠናቋል ብለዋል። የአረርቲ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ መሳይ አስታጥቄ በከተማው የኮሪደር ልማት ሥራን ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።   ልማቱንና የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማስመልከት ከከተማዋ ነዋሪዎች ጋር በስፋት ውይይት ተደርጎ የጋራ መግባባት ላይ መደረሱንም ጠቁመዋል። የእንሳሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አከበረኝ ዓለሙ በበኩላቸው እንደገለጹት ከሀገራዊ ለውጡ በፊት ተረስተው የቆዩ ከተሞች አሁን ላይ ትኩረት እያገኙ መሆናቸውን አስረድተዋል።   ለዚህም የለሚ ከተማ በኢንቨስትመንት እያደገች መምጣቷ አንዱ ማሳያ ነው ያሉት አቶ አከበረኝ፣ በአዲሱ በጀት ዓመት በከተማው የኮሪደር ልማትና የዲጂታላይዜሽን አሰራርን ለመጀመር ዝግጅት መደረጉን ጠቅስዋል። በውይይቱ ላይ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም እርስ በእርስ ለመማማር እና ምርቶቻችንን ለማስተዋወቅ እድል ፈጥሮልናል- አፍሪካውያን ስራ ፈጣሪ ወጣቶች
Jul 10, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት የተካሄደው ሶስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም እርስ በእርስ ለመማማርና ምርቶቻቸውን ለማስተዋወቅ ምቹ እድል እንደፈጠረላቸው አፍሪካውያን ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ተናገሩ። ላለፉት ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ትናንት ተጠናቋል። ከፎረሙ በተጓዳኝ በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ላይ ምርቶቻቸውን ያቀረቡ አፍሪካውያን ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ለኢዜአ እንዳሉት ፎረሙ ትስስርን ለመፍጠርና ምርቶቻቸውን በተሻለ መንገድ መስራት የሚችሉበት ግብዓት ያገኙበት ነው። ከኡጋንዳ የመጣችው የኢማሮ ኢኖቬሽን መስራች ካይክራ ባርብራ እንዳለችው በግብርና ምርቶች ላይ እሴት በመጨመር ወደገበያ እያቀረበች ትገኛለች።   በኢትዮጵያ በተካሄደው የሶስተኛው አፍሪካ የስራ እድል ፈጠራ ፎረም መሳተፏ ትስስርን በመፍጠር የምርት ጥራትን ለማሻሻል እንደሚያስችላት ገልፃለች። ከዚምባብዌ የመጣችው የማጅስቲክ አፍሪካ ዳይሬክተር ጌትሩድ ቻምባቲ በበኩሏ በግብርና ምርት ማቀነባበር ላይ ተሰማርታ ምርቶችን ለገበያ እያቀረበች መሆኑን ተናግራለች።   የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ከገበያ ትስስር ባለፈ እርስ በእርስ ለመማማር እድል የፈጠራና ምርቶችን ለማስተዋወቅ ያስቻላት መሆኑንም ገልፃለች። ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑን የገለጹት ተሳታፊዎቹ፤ አገሪቱ በፈጣን እድገት ላይ መሆኗን መመልከታቸውንም ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ለወጣቶች ስራ እድል ፈጠራ ምቹ የሆኑ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አስተውለናልም ብለዋል፡፡
በማዘጋጃ ቤቱ የተጀመረው ዘመናዊ አሰራር መጉላላትን አስቀርቶልናል - የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች
Jul 10, 2025 102
ሆሳዕና፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በሆሳዕና ከተማ ማዘጋጃ ቤት በአንድ ማዕከል አገልግሎት የተጀመረው ዘመናዊ አሰራር ሲገጥማቸው የነበረውን መጉላላት እንዳስቀረላቸው ነዋሪዎች ገለጹ። የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በበኩሉ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተገልጋይ እርካታን ለማምጣት የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። የሆሳዕና ከተማ ነዋሪ አቶ ሰላሙ አኒቶ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ከዚህ ቀደም በከተማው ማዘጋጃ ቤት ሲሰጥ የነበረው አገልግሎት ያልዘመነ በመሆኑ የተለያዩ ችግሮች ይገጥማቸው እንደነበር አስታውሰዋል። ቀደም ሲል የመረጃ አያያዙ በወረቀት ብቻ ያተኮረ በመሆኑ የፋይል መጥፋትን ጨምሮ የተለያዩ ችግሮች እየተከሰቱ ጉዳያቸውን ለማስፈጸም መጉላላት ይደርስባቸው እንደነበር ተናግረዋል። መረጃውን ለማፈላለግ በሚባክነው ጊዜና ጉልበት ነዋሪዎች ለእንግልትና ለሙስና ሲዳረጉ መቆየታቸውንም እንዲሁ። በአሁኑ ወቅት በከተማው በቴክኖሎጂ ታግዞ የተጀመረው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከሰው ንክኪ ውጭ መሆኑ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት ከማስቻሉ ባለፈ ይገጥማቸው የነበረን እንግልት እንዳስቀረላቸው ተናግረዋል።   ከዚህ ቀደም አገልግሎት ፈልጎ ወደ ማዘጋጃ ቤቱ የሚመጣ ነዋሪ የራሱን ማህደር እንኳ ለማግኘት መጉላላት ይገጥመው እንደነበር ያስታወሱት ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ክብነሽ ሶዲሶ ናቸው። በአግባቡ የተሰደረ የመረጃ አያያዝ ስላልነበረ ጉዳይ ለማስፈጸም ለበርካታ ጊዜ በመመላለስ እንጉላላ ነበር ያሉት ነዋሪዋ፣ ለቅሬታቸው በቂ መልስ የሚሰጥ ሰው ባለመኖሩም ጉዳይን ከሙስና ውጭ ለማስጨረስ ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰዋል። ማዘጋጃ ቤቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዲጂታል የታገዘ ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ፈጣንና ተገቢ አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ መፈጸማቸውን ተናግረው፣ የመልካም አስተዳደር ችግርን በመፍታት የተጀመረው ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲጠናከርም ጠይቀዋል።   በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማና ኢንደስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ስንታየሁ ወልደሚካኤል ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በክልሉ በማዘጋጃ ቤት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማረም ትኩረት ተሰጥቷል፡፡ በዚህም አገልግሎት አሰጣጡን የማዘመን ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ በዚህም የሆሳዕና ከተማን ጨምሮ በክልሉ አራት ከተሞች ሙሉ በመሉ በዲጂታል የታገዘ አገልግሎት እንዲሰጡ መደረጉንና ተስፋ ሰጪ ውጤት መታየቱን ተናግረዋል። የአገልግሎት አሰጣጡ መዘመኑ ከዚህ ቀደም በተገልጋዮች ላይ ይደርስ የነበረን እንግልትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍታት እንዳስቻለም ገልጸዋል። የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትን በማዘመን የተገልጋዩን እንግልት ለመቀነስ የተጀመረው ሥራ በቀጣይም በክልሉ የተለያዩ ከተሞች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ ስንታየሁ አስታውቀዋል፡፡ ዘንድሮ በክልሉ በ16 ከተሞች ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ለህብረተሰቡ ፍትሀዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ በተለይም መሬትና መሬት ነክ አገልግሎት፣ የግንባታ ፍቃድ እንዲሁም ከልዩ ልዩ አገልግሎት የሚሰበሰብ ክፍያና መሰል አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝድ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ነው ያስረዱት።    
ስፖርት
የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ዙር የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ 
Jul 11, 2025 69
  አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የሰባተኛ ቀን ውሎ የምድብ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምዕራብ አፍሪካውያኑ ጋና እና ማሊ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ በቤርካኔ ሙኒሲፓል ስታዲየም ይጫወታሉ። ጋና በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በደቡብ አፍሪካ የ2 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። ማሊ በበኩሏ ታንዛንያን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ጋና በውድድሩ ለመቆየት የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ ይኖርባታል። በአንጻሩ ማሊ ድል ከቀናት ሩብ ፍጻሜውን ትቀላቀላለች።   ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም አምስት ጊዜ እርስ በእርስ ተጫውተው ጋና ሶስት ጊዜ ስታሸንፍ ማሊ አንድ ጊዜ ድል ቀንቷታል። በቀሪው ጨዋታ ነጥብ ተጋርተዋል። በጨዋታዎቹ ጋና 15 ግቦችን ከመረብ ጋር ስታገናኝ ማሊ 12 ግቦችን አስቆጥራለች። ባላቸው የእርስ በእርስ ታሪክ ጋና የተሻለ የማሸነፍ ግምት ብታገኝም በጥሩ ወቅታዊ ብቃት ላይ የምትገኘው ማሊ ተጋጣሚዋን የመፈተን አቅም አላት። በዚሁ ምድብ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ታንዛንያ ከደቡብ አፍሪካ በሆነር ስታዲየም ይጫወታሉ። ደቡብ አፍሪካ በሶስት ነጥብ ምድቡን እየመራች ነው። ታንዛንያ ያለ ምንም ነጥብ በአንድ የግብ እዳ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት ደቡብ አፍሪካ ካሸነፈች ሩብ ፍጻሜ ትገባለች። ታንዛንያ በውድድሩ የመጀመሪያ ድሏን ለማስመዝገብ ጠንካራ ተጋጣሚዋን መርታት ይኖርባታል። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ ተገናኝተው ደቡብ አፍሪካ ሶስት ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዛለች። በቀሪው ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። ደቡብ አፍሪካ በጨዋታዎቹ ስምንት ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ታንዛንያ ሶስት ግቦችን አስቆጥራለች።
ናይጄሪያ ለሩብ ፍጻሜ አለፈች
Jul 11, 2025 76
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በ13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሶስት መርሃ ግብር ናይጄሪያ ቦትስዋናን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በላርቢ ዛውሊ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አጥቂዋ ቺንዌንዱ ለሄዙ በ89ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥራለች። ናይጄሪያ በጨዋታው ባደረገችው የመጀመሪያ ኢላማውን የጠበቀ የግብ ሙከራ ነው ጎል ማስቆጠር የቻለችው። በጨዋታው ጠንካራ ፉክክር የተደረገ ሲሆን ቦትስዋና የዘጠኝ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ናይጄሪያን ፈትናታለች። ውጤቱን ተከትሎ ናይጄሪያ በስድስት ነጥብ አንድ ጨዋታ እየቀራት ለሩብ ፍጻሜ አልፋለች። ቡድኑ ወደ ቀጣዩ ዙር ቢሸጋገርም የማጥቃት ድክመቱን ማረም እንደሚጠበቅበት በመገለጽ ላይ ይገኛል። ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ቦትስዋና ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛለች። በዚሁ ምድብ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ቱኒዚያ እና አልጄሪያ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል። አልጄሪያ በአራት ነጥብ ሁለተኛ እና ቱኒዚያ በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። ናይጄሪያን ከአልጄሪያ፣ ቱኒዚያ ከቦትስዋና የፊታችን እሁድ ሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ.ም የሚደረጉ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዎች ናቸው። በሶስት ምድብ ተከፍሎ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው 13ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ከየምድቡ አንደኛ እና ሁለተኛ የሚወጡ ሀገራት ለሩብ ፍጻሜ ያልፋሉ። ከምድቦቹ ምርጥ ሶስተኛ ሆነው የሚያጠናቅቁ ተጨማሪ ሁለት ሀገራት ሩብ ፍጻሜውን ይቀላቀላሉ።
አካባቢ ጥበቃ
ማዕከሉ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸው የላቀ ችግኞችን ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ ነው
Jul 11, 2025 66
ቴፒ፣ ሐምሌ 4/2017 (ኢዜአ)፡- የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸው የላቀ የቅመማ ቅመምና ፍራፍሬ ችግኞችን ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑን አስታወቀ። ማዕከሉ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ችግኞችን በማዘጋጀት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እንዲተከሉ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አስታውቋል። የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ደረጀ ቱሉ (ዶ/ር) ማዕከሉ ዘንድሮ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በማዘጋጀት በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እንዲተከሉ ለተለያዩ ክልሎች እያሰራጨ መሆኑን ገልጸዋል።   በአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር እንዲተከሉ ከተዘጋጁ ችግኞች መካከል ቡና፣ ካካዎ፣ አቮካዶ፣ ሻኔላና ሌሎችን ጨምሮ 8 ከደን ጋር በቀጥታ ተስማሚና ተያያዥነት ያላቸው እንደሚጠቀሱ ገልፀዋል። ማዕከሉ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል እያደረገች ባለው ጥረት ውስጥ ኢኮኖሚያዊ ጥቅማቸው የጎላ በምርምር የተደገፉ የሰብል አይነቶችን በማሰራጨት ረገድ ሚናውን እንዲሚያጠናክርም አረጋግጠዋል። በአካባቢው የሚመረቱ የቅመማ ቅመም ዓይነቶች ከዛፍ ጋር ግንኙነት ያላቸው በመሆኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከቅመም ልማት ነጥሎ ማየት እንደማይቻል ያነሱት ደግሞ የሸካ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ አዳምሰገድ ኃይለኢየሱስ ናቸው። በዚህም ባለፉት ሰባት ዓመታት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል በተሠራው ሥራ በዞኑ የደን ልማት ከምርታማነት ጋር አብሮ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። የየኪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ተሰማ በበኩላቸው በአረንጓዴ አሻራ ልማት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥም ቴክኖሎጂን በማስደገፍ የተገኙ ምርጥ የፍራፍሬ እና የቅመማ ቅመም ችግኞችን ከማዕከሉ በመውሰድ እየተከሉ መሆኑን ገልፀዋል። ችግኞቹ በአርሶ አደሮች ጓሮ እየተተከሉ መሆኑን ጠቁመው በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርት በመስጠትም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ሥነ-ምህዳራዊ ጥበቃን እውን በማድረግ ረገድ ሚናቸው የጎላ ነው ብለዋል።   በወረዳው የፊዴ ቀበሌ አርሶ አደር ዓይናቸው ካሳሁን እንዳሉት፤ በየዓመቱ የግራቪላ ችግኞችን በመትከል ከሥሩ የቁንዶ በርበሬ ቅመም በመትከል ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መጥቷል። ባለፉት አምስት ዓመታት ከ2 ሄክታር በላይ የቁንዶ በርበሬ ቅመምን በግራቪላ ችግኞች ስር በመትከል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀው ዘንድሮም ግማሽ ሄክታር ያህል ችግኝ የሚተከልበት ቦታ ማዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል፡፡      
ፅዱ ኢትዮጵያን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የመገናኛ ብዙሃን ሚና ወሳኝ ነው-ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ
Jul 11, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ፅዱ ኢትዮጵያን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የመገናኛ ብዙሃን ሚና ወሳኝ መሆኑን የኢትዮጵያ አካባቢ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጋር በመተባበር ሁለተኛው ዙር “የጽዱ ኢትዮጵያን ባህል ማድረግ” በሚል መሪ ሀሳብ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ላይ ለሁሉም የሚዲያ ባለሙያዎች እና ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።   በመድረኩ ላይ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ፣ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሚ፣ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙሃን አመራርና ባለሙያዎች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ እንዳሉት፥ መንግስት ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በተያያዘ ባለፉት ሰባት ዓመታት ሰፋፊ የልማት ስራዎች ማከናወኑን ተናግረዋል። የኮሪደር ልማት፣ አረንጓዴ አሻራና የወንዝ ዳርቻ የልማት ስራዎች በስፋት መሰራታቸውንም በማሳያነት አንስተዋል። አዲሱ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ በብክለት ምክንያት በአካባቢና በሰዎች ደህንነትና ጤና ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። ለአካባቢ ብክለት የሚዳርጉ እና አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ ስስ የፕላስቲክ ምርቶችን መጠቀም ላይ ክልክላ በማድረግ በሥርዓተ ምህዳር ላይ የሚያደርሱትን ጉዳት መከላከል እንደሚያስችል አብራርተዋል። አምራቾች ከማምረት ባሻገር ብክለትን በመከላከል ረገድ የራሳቸውን ሃላፊነት እንዲወጡ በማድረግ በኩል እድል የሚሰጥ ሰለመሆኑ ገልጸዋል። ፅዱ ኢትዮጵያን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የመገናኛ ብዙሃን ሚና ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል። የአካባቢ ጥበቃ ስራ የሁሉም ህብረተሰብ ክፍል ተሳትፎን እንደሚጠይቅ ጠቅሰው፥ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ የሚዲያ አካላት ድርሻ ወሳኝ እንደሆነ አክለዋል።   የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ በበኩላቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ ስራ ኢትዮጵያ ትኩረት ሰጥታ ከምትሰራቸው የልማት ተግባራት መካከል አንዱና ዋነኛው መሆኑን አንስተዋል። የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ፅዱ ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ ፕላስቲክን በወረቀት ለመተካት የተጀመረው ስራም እንደ ሀገር አዲስ ልምድ እና የሚደነቅ ተነሳሽነት መሆኑን ገልጸዋል። ለተግባራዊነቱና ለስኬቱም መገናኛ ብዙሃን ትክክለኛና ግንዛቤ የሚፈጥሩ መረጃዎችን ተደራሽ የማድረግ ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው አፅንኦት ሰጥተዋል። በብክለት ሳቢያ የሚደርሱ የጤና እክሎችን ቀድሞ በመከላከል የበለጸገችና ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ዜጋ የአካባቢ ጥበቃ አምባሳደር መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። በስልጠናው የተሳተፉ የሚዲያ ባለሙያዎች በበኩላቸው፤ የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ከተጀመረ ጀምሮ ለህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት በኩል ሚናቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡   በፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የዜና ክፍል አርታኢ የሆነው ምንይችል አዘዘው፤ ጽዱ ኢትዮጵያን በተመለከተ የተለያዩ ዘገባዎችን በመስራት ለህብረተሰቡ ተደራሽ እያደረገ መሆኑን አንስቷል፡፡ የዛሬው ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናም በቀጣይ በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ለሚያከናውናቸው የዘገባ ስራዎች ተጨማሪ አቅም እንደፈጠረለት ገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አዲስ ዘመን ጋዜጣ አዘጋጅ ታምራት ተስፋዬ በበኩሉ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የአካባቢ ጥበቃን በተመለከተ የወጡ አዳዲስ ህጎችን ህብረተሰቡ እንዲገነዘብ የበኩላችንን መወጣት አለብን ብሏል።   ጽዱ ኢትዮጵያን ለማሳካት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ፣ የፕላስቲክ ምርቶች አጠቃቀም እና አወጋገድን በሚመለከት የተቀመጡ ድንጋጌዎች እና አተገባበሩ ላይ በትኩረት እንደሚዘግብም ጠቁሟል።    
አረንጓዴ አሻራ ግድቦች እና ሐይቆች በደለል እንዳይሞሉ ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው-የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር
Jul 11, 2025 76
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ግድቦች እና ሐይቆች በደለል እንዳይሞሉና የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጨምር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል።   የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በስሩ የሚገኙ ተጠሪ ተቋማት ዛሬ ማለዳ በኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ግቢ የችግኝ ተከላ አካሂደዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዘርፈ ብዙ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። መርሃ ግብሩ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ምንጮችን በማጎልበት፣ የዝናብ ውሃን በማስረግ የከርሰ ምድር ውሃ ከፍ እንዲል በማድረግ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። የአፈር መሸርሸርን በመከላከል የገጸ ምድር የውሃ ሀብትን በመጠበቅም ግድቦች እና ሐይቆች በደለል እንዳይሞሉ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል።   የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ዋና ስራ አስፈጻሚ አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር)፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በየዓመቱ እየተጠናከረ መምጣቱን ተናግረዋል። መርሃ ግብሩ በተለይም በዓባይ ተፋሰስ ችግኝ በመትከል ህዳሴ ግድብን ከደለል ለመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ታመነ ሃይሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው መርሃ ግብሩ የውሃ ሀብትን ለማጎልበት እንደሚያስችል ተናግረዋል። መርሃ ግብሩ ጎርፍ እንዳይከሰት እና አፈር እንዳይሸረሸር በማድረግ ስነ ምህዳርን ለመጠበቅ የማይተካ ሚና እንዳለው የገለጹት የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፈጠነ ተሾመ ናቸው።   በ2017 የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል በማቀድ በመላ ሀገሪቱ የተጠናከረ የችግኝ ተከላ እየተከናወነ ይገኛል።    
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ሀብት እንዲያንሰራራ እያደረገ ነው - ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Jul 11, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2017(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የስርዓተ ምህዳር ጥበቃን በማጠናከር የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ሀብት እንዲያንሰራራ እያደረገ መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ፡፡ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እና የፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ሠራተኞች በየካ ተራራ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡ ፕሬዚዳንት ታዬ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በርካታ ትሩፋቶችን እያስገኘ እንደሚገኝ አንስተዋል።   የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰው፥ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ዕውቅና እንድታገኝ ያስቻለ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በርካታ ጠቀሜታዎችን በማስገኘት ላይ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፥ የተራቆተ የአካባቢ ስርዓተ ምህዳር እንዲታደስ እና እንዲለመልም እያደረገ ነው ብለዋል። የመሬት መንሸራተትን በመከላከልና የውሃ ሃብትን በመጠበቅ በኩልም ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት እያገዘ መሆኑን ጠቁመው በአፍሪካ በርሃማነትን ለመከላከል አርዓያነት ያለው ተነሳሽነት እንደሆነም አፅንኦት ሰጥተዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ተመናምኖ የነበረው የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ሀብት እንዲያንሰራራ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከሰው ልጅ ህይወት ጋር የተሳሰረ ነው ብለዋል። በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መሳተፍ ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር የማስረከብ ሀገራዊ አጀንዳ በመሆኑ፥ ሁሉም ህብረተሰብ ችግኝ በመትከል እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለመርሐ ግብሩ ስኬታማነት ከሐሳብ ማመንጨት እስከ ትግበራ እያደረጉ ላሉት የመሪነት ሚና ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል። በዚህ በ7ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃም 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዷል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 868
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ።   በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1286
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል።   የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 955
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል።   ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1581
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
የህንድ የፈጠራ ማዕከል - ባንጋሎሩ
Jul 2, 2025 386
ቤተልሄም ባህሩ(ኢዜአ) የዴልሂና አግራ ቆይታችንን ጨርሰን ወደ ቀጣይ መዳረሻችን ባንጋሎሩ ከተማ ልንጓዝ ስንሰናዳ አብዛኛው የጋዜጠኛ ልዑክ ያሳሰበው እንደሰም የምታቀልጠውን የአግራ ፀሀይና ሙቀት በባንጋሎሩም ታገኘን ይሆን? የሚለው ነበር። ሆኖም ከዴልሂ ኢንድራ ጋንዲ አየር ማረፊያ ተነስተን ለሶስት ሰዓት ከተቃረበ በረራ በኋላ ያገኘናት ባንጋሎሩ የተለየች ሆነን አገኘናት። ባንጋሎሩ ቀዝቀዝ ባለ አየር ነበር እንግዶቿን የተቀበለችን። በዕለቱ ከክፍሎቻችን ወጥተን በጋራ ወደአየር ማረፊያ የሚወስደንን ትራንስፖርት ስንጠባበቅ ከጋዜጠኛ ቡድኑ ስድስት አባላት ከአጠገባችን እንዳልነበሩ አስተዋልን። የት ጋር እንደተነጣጠልን አላስታውስም። በዚህ ምክንያት ግን የእለቱ ጉዟችን ተሰርዞ ከተማዋን ለማየት ስንዘዋወር የማውቀው ዓይነት እንጂ የተለየ ሙቀት አላስተናገድኩም። የ13 ወር ፀጋ በመባል የምትታወቀው አገሬ ኢትዮጵያ ከዳሎል እስከ ራስ ዳሽን ባላት የመልከዓ ምድር አቀማመጥና ልዩ ልዩ የአየር ጠባይ ሙቀቱንም፣ ቅዝቃዜውንም ማወቃችን እንደዚህ ለአለ አጋጣሚ መልካም ስሜት ይፈጥራል። በተወሰነ ደረጃ በህንድ ያጋጠመኝ የአየር ባህሪ ከአገሬ ጋር ቢመሳሰልብኝ የፈጣሪንና የተፈጥሮን ስራ አጃኢብ ብዬ እንዳልፍ አድርጎኛል። ባንጋሎሩ ከተማ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ማዕከል በመሆኗ የህንድ ሲልከን ቫሊ በመባል ትታወቃለች። ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ስፍራዎችም ከመገለጫዎቿ መካከል ናቸው። የጠፈር ጠበብቶቹ - ባንጋሎሩ ደርሰን በመጀመሪያ ያየነው ዓለም በስፔስ ሳይንስ እየሰራች ያለችውና እያስመዘገበችው የምትገኘው ውጤት ማሳያ የሆነውን የህንድ ስፔስ ምርምር ድርጅትን ነው። ተቋሙ የህንድ መንግስት የስፔስ ዲፓርትመንት አካል ሲሆን፤ ዶክተር ቪክራም ሳራብሃይ በተሰኙ ባለራዕይ በ1962 የተወጠነና አሁን ላይ በዘርፉ ተገዳዳሪ መሆን የቻለ ነው። የተቋሙ ዓላማ የስፔስ ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመተግበር ለተለያዩ አገራዊ ጥቅሞች ማዋል መሆኑን ተከትሎ የሳተላይት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማምረት ስራን ጨምሮ ከአገሩ አልፎ ለሌሎች አገራትም በዘርፉ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። የተደረገልን ገለፃ አብዛኛውን ጋዜጠኛ ያስደመመ ነበር ከገለፃ በኋላ በጋዜጠኞች የተነሳው ሃሳብም ህንድ በስፔስ ዘርፍ ያላት ልምድና ያከናወነችው ተግባር በቀጣይም ልትሰራ የወጠነቻቸው ሃሳቦች የአገሪቱን መዳረሻ የተለሙ በአገራቸው እንዲተገበር የሚናፍቁት መሆኑን ነው። ተቋሙ በዘርፉ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም ትብብሩን የሚያጠናክር መሆኑን ከተደረገልን ገለፃ ተገንዝበናል።   በሳይንስ፣ ኢንጂነሪንግና አስተዳደር ምሁራንን በማስተማር እያበረከተ ያለው የህንድ የሳይንስ ኢንስቲትዩት በባንጋሎሩ ከጎበኘናቸው መካከል የሚጠቀስ ነው። ኢንስቲትዩቱ ከአፍሪካ የተውጣጡ ተማሪዎችን የሚያስተምርና ከተቋማት ጋርም በዘርፉ የሚሰራ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ከጅማ፣ በተግባር ለመቀየር ሲታትሩ የስታርት አፖችን የምርት ውጤቶቻቸውን ሲፈትሹና ሲሞክሩ ተመልክቻለሁ። በኢትዮጵያም አሁን ላይ ለስታርት አፖች በተሰጠው ትኩረትና በተፈጠረው ምቹ ስነ ምህዳር የፈጠራ ውጤቶች እያደጉና እየተበራከቱ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። እንደ አዳማና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተቋማት የተማሪዎችን ፈጠራ ወደ ውጤት ለመቀየር እየተጉ መሆኑና የስታርት አፕ ኤግዚቢሽንና የሰመር ቡት ካምፖች ፈጠራን ምን ያህል እያበራከቱ መሆናቸው በጉብኝቱ ወቅት ወደ አዕምሮዬ የመጣ የአገሬው ህዝብ በውጤት የታጀበ ጥረት ነው።   ከአራት አስርት ዓመታት በላይ በባዩቴክኖሎጂ ዘርፍ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኘው ባዮኮንም ከባላንጎሩ የጉብኝት መዳረሻችን መካከል የሆነና አስፈላጊ መድሀኒቶችን የሚያመርትና በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይም እየሰራ ያለ ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት የአቅም ግንባታ ስልጠናው ተጠቃሚ ናቸው። ከ120 በላይ በሆኑ አገራት ለስኳርና ካንሰር ህመም የሚያገለገሉ መድሀኒቶችን በማምረትና በማሰራጨት ለህሙማን ፈውስና ለጤናው ዘርፍ ስርዓት አስተዋፅኦ እያበረከተም ይገኛል። የተቋሙ ላቦራቶሪና ዘመኑን የዋጀና ደረጃውን የጠበቀ ማምረቻ ፋብሪካን መጎብኘቴ አለም በፋርማሲዩቲካልስ ዘርፍ ያለችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። የባንጋሎሩ ቤተመንግስት - ይህን ቤተ መንግስት ማስቃኘቴን ከመጀመሬ በፊት በስፍራው ካስገረመኝ ነገር ላወጋችሁ ወደድኩ። ቤተ መንግስቱን ለመጎብኘት ያቀናነው በእለተ ሰኞ ነበር። ሆኖም ምድረ ግቢውን ቃኝተን ስለህንፃው ሰምተን ከመመለስ ውጪ ወደ ውስጥ አልዘለቅንም። ለምን? ለሚለው ምላሹ በዚህ ስፍራ "ሰኞ የእረፍት ቀን ናት" ነው። እንዴት ካላችሁ ቤተ መንግስቱ ቅዳሜና እሁድ በበርካታ ሰዎች የሚጎበኝ መሆኑን ተከትሎ በስፍራው ለሚሰሩ ሰራተኞች የእረፍት ቀናቸው ሰኞ በመሆኑ ነው። የቤተ መንግስቱ ምድረ ግቢ ሰፊና ልምላሜ የተላበሰ ሲሆን፤ የሚያምርና ለዓይን የሚስብ ኪነ ህንፃ ያለው ነው። አሰራሩና ውጥኑም እንደሚከተለው ነው። በዎዲየር ስርወ መንግስት ንጉስ ቻማራጃ ዋዲያር ወደ እንግሊዝ ባደረጉት ጉዞ በለንደን ዊንሶር ግንብ ይደነቃል። ተደንቆም አልቀረ የባንጋሎሩ ቤተ መንግስትን በተመሳሳይ ሁኔታ ይገነባል። ይህ ቤተ መንግስት በተወሰነ መልኩ የመካከለኛው ዘመን የኖርማንሲና የእንግሊዝ ግንቦችን ይመስላል።   ቪድሃና ሶውዳ የካራንታካ ህግ አውጪ አካል መናገሻ በጉብኝታችን ያየነው ሌላው መዳረሻ ስፍራችን ነው። የህግ አውጪና የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የያዘው ይህ ህንፃ ህንድ ነፃነቷን ካገኘች በኋላ በራሷ መሀንዲስ የሰራችው የመጀመሪያው ህንፃ መሆኑ ተገልፆልናል። የህንፃ ግንባታ ጥበብ ማሳያ፣ የፖለቲካ መናገሻ እንዲሁም የባህል ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል።   እንደአጠቃላይ በቆይታዬ የተመለከትኩት የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ማበረታቻ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራ ኢትዮጵያ እያከናወነች ካለው የኮሪደር ልማትና ስታርት አፕን የማበረታታት ብሎም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስነ ምህዳር ምቹነት ስራዎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ነው። በህንድና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ዘመናትን የተሻገረ፤ ለሁለት ሺህ ዓመታት የዘለቀ መሆኑን የታሪክ መዛግብት ያሳያል። የህንድና ኢትዮጵያ ግንኙነት በአክሱም ስርወ መንግስት ኢትዮጵያና ህንድ በአዱሊስ ወደብ በኩል የንግድ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። በወቅቱ ኢትዮጵያ ቅመማ ቅመምና ሐርን ከህንድ ትገበይ ነበር። ህንድ ደግሞ ወርቅና የዝሆን ጥርስን ከኢትዮጵያ ትሸምት ነበር። ህንድ ከንግድ ልውውጥ ባሻገር በኢትዮጵያ ኪነ ህንፃ ግንባታ ላይ አሻራዋን አኑራለች። በኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍም ትልቅ አበርክቶ ያላት አገር ናት። ህንድ ነፃነቷን ካገኘችበት እኤአ 1948 አንስቶ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት ኢትዮጵያና ህንድ ሌላው የሚያመሳስላቸው ነገር ሆኖ ያገኘሁት የአምራች ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እያከናወኑ ያሉት ንቅናቄ ነው። ህንድ እ.አ.አ ከ2014 ጀምሮ የአምራች ዘርፉን ለማበረታታት "ሜድ ኢን ኢንዲያ" በሚል ለአስር ዓመት የተገበረችውና በርካታ ለውጥ የተመዘገበበት ንቅናቄ በኢትዮጵያ ከ2014ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ካለውና የሃገር በቀል ምርቶች እና አምራቾችን ማጠናከር፣ የኢንዱስትሪያል ማህበረሰብ ግንባታን ማሳደግ ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢ መፍጠር እና የጥናት እና ምርምር ችግር ፈቺነትን ማሳደግን ዓላማ ካደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ጋር የተመሳሰለ ነው። ንቅናቄ በኢትዮጵያ መተግበሩ ዓመታዊ የዘርፍ ዕድገት፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና ገቢ ምርት በመተካት በኩል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑም ይታወቃል። በህንድ ተዘዋውሬ በተመለከትካቸው ከተማዎች ባሉ ጎዳናዎች ከታዘብኩት ነገር ሰዎች ከሱቅ ለሚገበያዩት ነገር ሳይቀር በዲጂታል መንገድ ክፍያ መፈፀማቸውን ነው። በባጃጅና በሞተር የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘትም ጭምር ሞባይሉን በመጠቀም “ይህ ቦታ የት ነው?” ሳይል ያሻዎት ስፍራ መድረስም ሌላው ትዝብቴ ነው። ይህ ነገር በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትኩረት አግኝተው እየተሰራባቸው ካሉት የዲጂታል ክፍያና ዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ መርሃ ግብር ጋር የሚመሳሰል ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በቆይታችን ልክ እንደአትሌቶቻችን ሁሉ በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ አድርጎ የሚያስነሳውን ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዝናና ክብር ለማስተዋል ችያለሁ። ፀጉረ ልውጥ መሆናችንን የተገነዘቡ በገበያ ማዕከላት የሚያገኙን እንዲሁም በምንጎበኛቸው ተቋማት የምንተዋወቃቸው ህንዳውያን "ከየት ናችሁ?" ብለው ሲጠይቁ፤ ለእኔና አንድ ከሌላ መገናኛ ብዙሃን የሄድን "ከኢትዮጵያዊ" ስንል የሚከተልልን ምላሽ "አሃ የኢትዮጵያ አየር መንገድ" የሚል ነው። ይህም አየር መንገዱ ስሙ ከኢትዮጵያ ተሰናስሎ የሚጠራ የአገሪቷ መታወቂያ ተቋም መሆኑን ያስገነዘበኝ ነው። ከህንዳውያን ጋር ብቻ ሳይሆን አብረን ከተጓዝን ጋዜጠኞች አንዱ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ የእናንተ የብቻ ሳይሆን እኛንም እንደራሳችን ሆኖ እያገለገለን ያለ የጋራ አየር መንገዳችን ነው" ሲል ነው የገለፀው። ይሄ ለእኔ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገር ኩራት ብቻ ሳይሆን መለያ ምልክትም ጭምር መሆኑን የተረዳሁበት አጋጣሚ ነው። በቀናት ቆይታዬ በእንግዳ አክባሪነታቸውና በለገሱን ፍቅርና እንክብካቤ ከአገሬ የራቅኩ ያህል ሳይሰማኝ ብቸኝነትን ሳላስተናግድ እንደውም እየናፈኳቸው እንድመለስ ላደረጉኝ ህንዳውያን በከበረ ሰላምታ ላመሰግን እወዳለሁ።
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 432
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል።   ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል።   የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው።   የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው።   ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።    
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 965
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች።   የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች።   ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ።   ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።      
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 1085
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 3332
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች።   የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።   ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።    
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት 
Dec 16, 2024 2779
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ​ ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። ​​​ አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። ​​​ አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ​​​ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ​​​ ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። ​​​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ​ እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 2959
    የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። ​ በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል።   ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 4088
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል።   ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2636
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2353
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3801
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል።     በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል።   የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48449
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43886
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 28051
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25400
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 23641
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 21774
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 21628
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 21256
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 48449
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 43886
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 28051
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 25400
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ከሮም እስከ አዲስ አበባ 
Jul 11, 2025 72
ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ይካሔዳል። የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ኢንቨስትመንት እና ፋይናንስ፣ የምግብ ስርዓት ሽግግር ሁለንተናዊነትና የተገቡ ቃሎችን ከመፈጸም አንጻር ያለውን የተጠያቂነት ስርዓት ማጠናከር ጉባኤው ትኩረት ያሚያደርግባቸው ሀሳቦች ናቸው። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተምግብ ጉባኤ በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በጣልያን ሮም የተካሄደው የመጀመሪያ የተመድ ስርዓት ምግብ ላይ የተገቡ ቃሎች ትግበራ ሂደትን መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ነው። በመጀመሪያው ጉባኤ ላይ የ182 ሀገራት ተወካዮች፣ 21 የሀገራት መሪዎች እና 126 ሚኒስትሮችን ጨምሮ 3 ሺህ 300 ተሳታፊዎች ታድመውበታል። በጉባኤው ላይ የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሀገራት እና ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ስድስት የትኩረት አቅጣጫዎችን ይፋ አድርገው ነበር።   የምግብ ስርዓት ስትራቴጂዎችን ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር፣ ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓት አስተዳደር መገንባት፣ በጥናት፣ ዳታ፣ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ ሁሉን አቀፍ የእቅድ ዝግጅት እና ትግበራን ማጠናከር፣ በምግብ ስርዓት ውስጥ የንግዱ ማህበረሰብ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የአጭርና የረጅም ጊዜ የአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ ከትኩረት አቅጣጫዎቹ መካከል ይጠቀሳሉ። ኢንቨስትመንት፣ የበጀት ድጋፍ እና የእዳ አስተዳደር ሌላኛው የትኩረት መስክ ነው። በጉባኤው ላይ 300 ገደማ በሚሆኑ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የምግብ ስርዓት ሽግግርን እውን ለማድረግ ቃል መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃ ያመለክታል። በተለይም እ.አ.አ 2030 የማይበገር፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የምግብ ስርዓት መገንባት እንዲሁም ምግብ ለሁሉም የሚለውን ግብ ለማሳካት ጥረት እንደሚያደርጉ ሀገራት ቃል ገብተዋል።   ሁሉን አሳታፊ ነው በሚል አድናቆት ያገኘው ጉባኤው በስርዓት ምግብ ላይ ግንዛቤን ከማሳደግ እና አቅምን ከመገንባት አንጻር ውጤታማ እንደነበር ይነሳል። የምግብ ስርዓት ሽግግር አንገብጋቢና ጊዜ የማይሰጥ ጉዳይ እንደሆነም በጉባኤው ተወስቷል። ኢትዮጵያም በስርዓተ-ምግብ ጉባኤው ላይ የነበራት ተሳትፎ ስኬታማ ነበር። በግብርናው ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ውጤታማ እንቅስቃሴዎችን የሚያሳዩ ልምደችን አቅርባለች። በጉባኤው ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ግብርናን በማዘመን የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥና በስርዓተ ምግብ ሽግግር ለማምጣት እየወሰደች ባለው የፖሊሲ እርምጃና ውጤቶች ዙሪያ ገለጻ አድርገውም ነበር። ኢትዮጵያ የኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት፣ ለየስነ ምህዳሩ ተስማሚ የሆኑ የተሻሻሉ ዝርያዎችን፣ አነስተኛ ቴክኖሎጂዎችንና ሌሎች ግብአቶችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለኢኮኖሚው ዕድገት የላቀ አበርክቶ እንዲኖረው እየሰራች መሆኑንም አንስተዋል።   በአረንጓዴ አሻራ፣ በበጋ መስኖ በተለይም በበጋ ስንዴ ምርት እና በሌማት ትሩፋት እየተገኙ ያሉ ውጤቶችን ለጉባኤው አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግብርና ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የስራ እድል ፈጠራን ለማበረታታትም ሆነ በስርዓተ-ምግብ ሽግግር ለማድረግ አዲስና የተለየ የፋይናንስ ሞዴል ያስፋልጋል በማለት በአጽንኦት ተናግረዋል። ዘላቂና አካታች የስርዓተ ምግብ ሽግግር አቅጣጫዎች ጥሩ አፈጻጸም የታየባቸው ቢሆንም በፋይናንስ አቅርቦት፣ በዓለም አቀፍ ትብብር፣ በአየር ንብረት ለውጥና በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመቋቋም በትብብር በመስራት በኩል በርካታ ችግሮች መስተዋላቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የገለጹት። በመሆኑም ሀገሮች በስርዓተ ምግብ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በአነስተኛ እርሻ ስር-ነቀል ለውጥ በማምጣት ሽግግሩን ማፋጠን እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፅንኦት አንስተዋል። ለዚህም የሴቶችና የወጣቶች ተሳትፎን እንዲያሳድጉና ለግብርና ቴክኖሎጂ መስፋፋት እንዲሰሩ ጠይቀዋል ። ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ-ምግብ ጉባኤ የመጀመሪያውን ጉባኤ መነሻ በማድረግ በተለያዩ አጀንዳዎች ይመክራል። ቀዳሚ ትኩረቱ ከመጀመሪያው ጉባኤው በኋላ የምግብ ስርዓትን አስመለክቶ ያሉ ለውጦች ምንድን ናቸው? የሚለው ነው። በጉባኤው ላይ ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን አስመልክቶ ያገኟቸውን ስኬቶች እና የጋጠሟቸው ተግዳሮቶች ላይ ሪፖርት ያቀርባሉ። በተለይም የምግብ ስርዓት ሽግግሩ ሁለንተናዊነት እና ሁሉን አሳታፊነት ዋንኛ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ሁለተኛው የጉባኤው አጀንዳ በመንግስታት፣ የምግብ አምራቾች፣ የንግድ ማህበረሰቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር ነው። የባለድርሻ አካላት ትብብር መጠናከር የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንዳለው ታምኖበታል። በተጨማሪም ሀገራት እና ተቋማት በሮሙ ጉባኤ የገቧቸው ቃሎች የደረሱበትን ደረጃ የሚገመገም ሲሆን ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎም ይጠበቃል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት እና የኢንቨስትመንት መጠንን መጨመር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ጉባኤው ይመክራል። ለምግብ ስርዓት ሽግግር ስራዎች በአነስተኛ ወለድ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ፣ አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም እና ሀገር በቀል የፋይናንስ መሰብሰብ አቅምን ማጎልበት ላይ ምክክሮች ይደረጋሉ ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ በሮም በነበረው ጉባኤው ላይ ይፋ ያደረጓቸው ስድስት የትኩረት መስኮች አፈጻጸም ግምገማ ሌላኛው አጀንዳ ነው። በአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባ የሚካሄደው ሁለተኛው የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ የሀገራት መሪዎች እና ተወካዮች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ አርሶ አደሮች፣ አምራቾች እና የምግብ ስርዓት ሽግግር ተዋንያንን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። በጉባኤው ላይ ከዋናው ሁነት ጎን ለጎን የምግብ ስርዓት ትራስፎርሜሽን እና የስርዓተ ምግብ ሽግግርን አስመልክቶ በርካታ የጎንዮሽ ስብስባዎች ይደረጋሉ። ኢትዮጵያ በምግብ ስርዓት ሽግግር ያከናወናቸውን ስራዎች አስመልክቶም በጉባኤው ተሳታፊዎች የመስክ ምልከታ ይደረጋል። ኢትዮጵያ በስርዓት ምግብ ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ እና በግብርናው ዘርፍ ባደረጋቻቸው ሀገር በቀል ሪፎርሞች ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ጉባኤውን እንድታስተናግድ የተመረጥችባቸው ምክንያቶች ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር እየተወጣች ያለው የመሪነት ሚና እና በማደግ ላይ ከሚገኙ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ተምሳሌት የሆነች ሀገር መሆኗ ተመድ ዓለም አቀፉን ከፍተኛ ጉባኤ በኢትዮጵያ እንዲያደርግ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። በጉባኤው ላይ ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግርን ለማሳካት እያከናወነች ባለው ተግባር ዙሪያ ተሞክሮዋን ለዓለም ማህበረሰብ የማስገንዘብ ስራ ታከናውናለች። ተባባሪ አዘጋጇ ጣልያን እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ በምግብ ስርዓት ሽግግር ውጤታማ ተሞክሮ ያላት ሀገር ናት። የደቡብ አውሮፓዊቷ ሀገር ከኢትዮዮጵያ ጋር በመሆን ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን እየሰራችም ትገኛለች። ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ተሳታፊዎች ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እየጠበቀች ትገኛለች።  
በቻይና ይህም አለ!
Jul 8, 2025 218
  በአብነት ታደሰ በርግጥ ከዓለማችን የጥንት ስልጣኔ ምድሮች አንዷ ናት- ቻይና። በታሪክ ገጾች ‘የግኝት ምድር’(Land of Invention) የሚል ተቀፅላ የሰፈረላት የሺህ ዘመናት ባለታሪክ ሀገር። የጥንት ቻይኖች አያሌ ‘ግኝቶችን’ ለዓለም አካፍለዋል። ወረቀት ፈብርከው ዘመናቸውን ጽፈዋል፣ ማተሚያ ቁስ ፈጥረው አትመዋል፤ ኮምፓስ ፈልስመው አቅጣጫ ጠቁመዋል።በ221 ዓመተ-ዓለም አንድ ወጥ ስርወ መንግስት መስርተው በሀገረ መንግስት የታሪክ ዑደት ከፍታንም ዝቅታንም አይተዋል። በቻይና አያሌ ስርወ መንግስታት ተፈራርቀዋል። ቻይናውያን ክፉውንም ደጉንም ችለው አልፋዋል። የሕዝቡ ጽናት፣ ጥበብ፣ ቱባ ባህል፣ ታሪክና ብልሃት በቻይና ግንብ ይመሰላል። ግንቡም ዝም ብሎ የጡብ ክምር አይደለም፤ የመሰረተ-ጽኑነታቸው ትዕምርት(symbol) እንጂ። ሲሶውን ሕዝቧ በያንግትዝ ወንዝ ተፋሰስ ጉያ አቅፋ፣ ጥንተ ማንነቷን ሸክፋ ዕልፍ ዘመናትን ተሻግራለች። የቻይና ስርወ መንግስታት ከስመው የዛሬዋ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ ቻይና ከተመሰረተች ገና አንድ ምዕተ ዓመቷ ነው። ቅድመ ልደተ ክርስቶት በ221 ዓመተ-ዓለም የተመሰረተው ወጥ-ስርዎ መንግስት በመልከ ብዙ ምክንያቶች ተዳከመ። በፈረንጆቹ 1912 የመጨረሻው የቻይና ስርዎ መንግስት ተንኮታኮተ። ዘመናዊቷ የቻይና ሪፐብሊክ በዚህ ዘመን ተመሰረተች። ዳሩ ለውጡ አልጋ በአልጋ አልሆነም። ለሺህ ዘመን የጽኑ ስርዓተ መንግስት ባለቤቷ ሀገር ቻይና በአስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት ታመሰች። ወረራንም፣ ዕልቂትንም አስተናገደች። በዘመኑ ማኦ ዘዶንግ የሚባል ባለራዕይ መሪ በቻይና ምድር ተነሳ። አርቆ አሰበ፤ ሀሳቡንም አሰረጸ፤ በዓላማ ጸንቶ ክፉ ዘመን ተሻገረ። ማኦ እና ተከታዮቹ ለቻይና ትንሳኤ ታተሩ። በጽናት ታገሉ። ለመስዕዋትነት ቆርጠው ተነሱ፤ ዋጋም ከፈሉ። በአውሮፓዊኑ ዘመን አቆጣጣር በ1949 የዛሬዋን የቻይና ሕዝባዊ ኮሚኒስት ሪፐብሊክ መሰረተ። ሃሳቡን ወደ ፖሊሲ ቀየረ፤ ተገበረውም። ቻይናን በኢንዱስትሪና ግብርና ምርት በንቅናቄ የማስፈንጠር ፕሮግራምንም (Great Leap Forward) ገቢራዊ አደረገ። ሆኖም ፖሊሲው በአንዴ ፍሬ አላፈራም። በወቅቱ በተፈጥሯዊና በሌሎች ምክንያቶች ቻይና በረሀብ ጠኔ ተመታች። ቻይናዊያን ተራቡ፤ ጎረቤት ሀገራትን ደጅ ጠኑ፤ ታላቁን ረሀብ መሻገር ያልቻሉ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቻይናዊያን በረሀብ አለቁ። በቻንግሻ የሚገኘው የማኦ ዘዶንግ ግዙፍ ሐውልት መራራ ጽዋን ተጎነጩ። የሀገሪቷ መሪ ማኦ ዘዶንግ በወቅቱ ፈተና ተስፋ ሳይቆርጥ ሀገር አሻጋሪ ፖሊሲውን ገቢራዊ አደረገ። ልመናን ለትውልድ ላለማውረስ፣ ንቅዘትን(ሙስናን) ነውር የሚያደርግ ስርዓት አጸና። ስራን ወንጌል፤ ሙስናን ወንጀል ያደረገ ጽኑ ስርዓተ መንግስት ገነባ። ከራሷ አልፋ ለዓለም የተረፈችዋን የዛሬዋን ቻይና በጽኑ መሰረት ላይ አነበረ። የዛሬዋ ቻይና ከዓለማችን ቁንጮ ልዕለ ሃያል ሀገራት አንዷ ናት። ከራሷ አልፋ ለዓለም ተርፋለች፤ የቻይና ቴክኖሎጂ ምጥቀትና ርቀት ዓለም ጉድ አሰኝቷል። በቅርቡ ሀገረ ቻይናን ከጎበኙ ጋዜጠኞች አንዷ ሆኜ ‘መልክዓ ቻይና’ን በወፍ በረር ቃኘሁ። በዚህ ማስታወሻዬ በቻይና የቴክኖሎጂ ልህቀትና ምጥቀት ላይ ብቻ አተኩራለሁ። ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ህዝብ ባላት፣ በ14 ሀገራት በምትዋሰነው፣ በአንድ ኮሚኒስት ፓርቲ በምትመራው ሀገር ቻይና በነበረኝ የ15 ቀናት ቆይታ ቻይና እንደ ጥንተ ታሪኳ ሁሉ በዘመኑ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ላይ ያላትን የመራቀቅ ጥግ ታዘብኩ። ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን የመቅደም እሽቅድድሟ ‘አጃይብ’ ያሰኛል። በሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና በማዕከላዊ ቻይዋ በምትገኘው የሁናን ግዛት ዋና ከተማ ቻንግሻ ምልከታዬ ቻይና ’ከተባለላት በላይ’ የቴክኖሎጂ ምጥቀቷ አስደንቆኛል። ምናልባትም የመጀመሪያ ጉዞዬ መሆኑም ነገሩን በአንክሮት እንድመለከት ሳያስገድደኝ አልቀረም። የሀገሪቷ ርዕሰ መዲና ቤጂንግ እና ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከ22 ሚለዮን የሚልቅ ህዝብ በጉያዋ የታቀፈችው ታላቋ ቤጂንግ ከተማ ከዓለማችን ግንባር ቀደም የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህል፣ የቱሪዝምና የዲፕሎማሲ ማዕከላት አንዷ ናት። የአዲስ አበባ እህት ከተማ በዚህ ወቅት ሞቃታማ አየር ጸባት አላት። ቤጂንግ የ21ኛው ክፍል ዘመን የኪነ ህንፃና ክትመት ቴክኖሎጂ ያበበች ብቻ አይደለችም፤ ይልቁኑም በዛፎች ሀመልማላዊ ገጽታ የተላበሰች ውብ መዲና እንጂ። በሕንፃዎችም፣ በዛፎችም የተደነነች ከተማ። በተፈጥሮ የበቀሉ የሚመስሉ ሰማይ ታካኪ ሕንጻዎች፤ የመንገድ መሰረተ ልማት ስፋት፣ ጽዳትና ጥራት ‘ኩልል’ ያለች፣ ‘ምልል’ የምታደርግ ከተማ ያደርጋታል። ቤጂንግ ከተማ ከዘመናችን አስደናቂ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አንዱ በሆነው የሰው ሰራሽ አስተውሎት(አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ) ሕይወትና ኑሮን እንዴት እንዳቃለለ የቤጂንግ የዕለት ከዕለት ክዋኔ ሁነኛ ማሳያ ነው። ቻይኖች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ተጠበዋል፤ መጠበብ ብቻም ሳይሆን ኑባሬያቸውን ሰው ሰራሽ አስተውሎት መር አድርገዋል። ከሮቦት መስተንግዶ እስከ ሰው ሰራሽ ፀሐይ መራቀቅ ይስተዋላል።   ካረፍኩበት ሆቴል (15ኛ ወለል ላይ ከሚገኘው መኝታ ክፍሌ) ሆኜ ያዘዝኩት ምግብ በቅጽበት አስተናጋጇ ‘ከች’ ብላ ትደውላለች። ፍጥነቷ ስትገረም፤ አስተናጋጆች ሮቦቶች መሆናቸውን ስትመለከት ይበልጥ ትደነቃለለህ። በክፍሌ ውስጥ ማብሪያ ማጥፊያ ስጫን መጋረጃው ሲከፈት መደንገጤን አልሸሽግም፣ ከምሽቱ 3 ሰዓት ፀሐይ አለመጥለቋን ስመለከት ‘የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ወጣች እንዴ?’ ማለቴ አልቀረም። በነገራችን ላይ የቻይና የሰው ሰራሽ ፀሐይ ሳይንሳዊ ፈጠራ ሁለት ግዜ ተሞክሮ ያለምንም እንከን እንደሚሰራ ነግረውናል። የሰው ሰራሽ ፀሐዩ ሃይድሮጅን እና ዱተሪየም ጋዞችን እንደ ሀይል ማመንጫ ነዳጅነት በመጠቀም ንጹህ ኢነርጂን ለማመንጨት ታስቦ ዲዛይን እንደተደረገና ሰው ሰራሽ ፀሐይ በርሐን ከተፈጥሮ ፀሐይ 13 እጥፍ ያክል ሙቀት እንደሚያመነጭም ሰምተን ተደንቀናል። የቻይና ሰው ሰራሽ ፀሐይ ፕሮጀክት የሥራ ሰዓትን ከ13 ሰዓት ወደ 24 ሰዓት ለመጨመርና ምርታማነትን ለማሳደግ ግብ የሰነቀ ነው። በቻይና በሰዉ ቅርፅ የተሰሩ ሮቦቶች በእግር ኳስ ጨዋታዎች ተወዳጅነት አትርፈዋል። ቤጂንግ የሚገኘው ሂዩማኖይድ የተሰኘ የሮቦት ቡድን የሰራቸው ሮቦቶች አመርቂ ውጤት ከራቀው የሀገሪቷ እግር ኳስ ቡድን ይልቅ የሀገሬውን ቀልብ እንደሳቡ ይነገራል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት በታገዘ የሮቦቶች ውድድር አያሌ ቻይናዊያን ይታደማሉ። ሮቦቶቹ በጨዋታ መሐል ቢወድቁ በራሳቸውን ይነሳሉ፤ ቢጎዱም ከሜዳ የሚወጡበት ስርዓት ተዘርግቷል። የታላቋ ቻይና ሰዎች ቴክኖሎጂን ከችግር መፍቻነት ወደ መዝናኛነትም አልቀውታል። በሀገራችን እንደ አዲስ ቴክኖሎጂ በንግዱ ስርዓት ውስጥ እየተዋወቀ ያለው የፈጣን ምላሽ መለያ ወይም ኪው አር ኮድ(Quick Response code) በቻይና ዕለታዊ ከዋኔዎች ቅንጦት አይደለም። በቻይና ማንኛውም ግልጋሎት በዚህ በዲጂታል ስርዓት ይከወናል። እንደሌሎች ስልጡን ሀገራት ሁሉ በንክኪ የሚደረግ ገንዘብ ዝውውር ቀርቷል። በቤጂንግ ጎዳናዎች በኪው አር ኮድ(QR Code) በሚንቀሳቀሱ ሞተር ሳይክሎችን በየመንገዱ ተሰድረዋል፤ የፈለገ መንገደኛ ሳይክሎችን በመጠቀም ወደ ፈለገበት ስፍራ ተንቀሳቅሶ ክፍያውን በኪው አር ኮድ ከፍሎ ይሄዳል። ሌላውም እንዲሁ። በአዲስ አበባ መኖሪያ ሰፈሬ የነበሩ ሳይክሎኝ ከደጃችን ደብዛቸው እንደጠፋ ሳስብ በቻይኖች ብልሃት፣ ታማኝነትና የከተሜነት ልህቀት ቀናሁ። በርግጥ በቻይና ኪው አር(QR) ኮድ ለተገለገልንበት መክፈያ ብቻ ሳይሆን ለልመናም መዋሉን ሲመለከቱ ፈገግ ሊሉ ይችላሉ። በቻይና ይህም አለ በማለት። በርግጥ በቤጂንግ የሰው እጅ ከሚያይ ይልቅ ጆሮቸውን ቢቆጥርጣቸው የሚሰሙ የማይመስሉ አዛውንቶች ሳይቀር በስራ ላይ ተጠምደው ይስተዋላሉ። ከቻይናውያን ጋር ለመግባባት በተለይም በንግድ ማዕከላት የቻይንኛ ቋንቋ መረዳት ግድ ይላል። “ሃው ማቺ፣ ጉዳ ጉዳ፤ ሺሼ፣ ኢ፣ አር…” እና መሰል ቃላት ማወቅ ይበጃል። ከዚህ ባለፈ በምልክት መግባባት አልያም በቋንቋ ተርጓሚ መተግበሪያ መጠቀም ያሻል። የቻይና ሰራሽ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምርቶች በራሳቸው ብራንድ፣ ቋንቋና መልክ እየተመረቱ በተመጣጣሽ ዋጋ ለህዝቦቿ ተደራሽ እየተደረጉ ነው። የቻይና የራስ-በቅነት ጥረት ያስቀናል። በቴክኖሎጂ፣ በባሕልና በኢኮኖሚ ተጽዕኖ ተላቀው በራሳቸው ለመቆም የሄዱበት ርቀት ግሩም ነው። ግብይቶች በራሳቸው ገንዘብ ብቻ ይከወናል። በወቅቱ ምንዛሬ አንድ የአሜሪካ ዶላር ሰባት የቻይና ገንዘብ(ዩዋን) ነው። ከምዕራባዊያን ማህበራዊ ትስስር ገጾች(ለምሳሌ ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ፣ ቲክቶክ) በሕግ በማገድ የራሳቸውን መተግበሪያ አበልጽገው ገቢራዊ አድርገዋል። ‘ዊቻት’ የተሰኘው መተግበሪያ ሁሉም ቻይናውያን መገልገያ ነው።   ከቤጂንግ ሌላ ያስደነቀችኝ ጥንታዊቷ ቻንግሻ ከተማ ነች። ቻንግሻ ስመ-ብዙ ነች። ከሶስት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ ጠገቧ የሁናን ግዛት ርዕሰ መዲና ቻንግሻ ‘የከዋክብት ከተማ’ ትሰኛለች። በነገራችን ላይ ማኦ ዘዶንግ ትውልዱ ሁናን ግዛት ውስጥ ነው። ቻንግሻ በስራ ከተማነቷ ‘የማታንቀላፋው መዲና’ ትባላለች። በመዝናኛ ስፍራነቷ ‘የተዝናኖት መነሃሪያ’ የሚል ተቀጥላ ስም አላት። ‘የሚዲያ ጥበብ’ ስፍራም ትሰኛለች። በኢንዱስትሪ፣ በጥንታዊ ሐውልቶች፣ አብያተ መቅደሶች፣ ታሪካዊ ስፍራዎች መገኛ በመሆኗ በቱሪስቶች ተወዳጅ ከተማ ናት። ትናንትና ዛሬን ያዋደደች፣ ታሪክና ባህል ባዛነቀችዋ ቻንግሻ የአምስት ቀናት ቆይታዬ ብዙ ገጽታዋ አስደምሞኛል። የሻንግ ወንዝን ተንተርሳ፣ በተራራማ፣ በሜዳማና ኮረብታማ መልክዓ ምድር በማዛነቅ የተቆረቆረች በመሆኗ የስብት ማዕከል ሆናለች። እንደ ቤጂንግ በደን የተከበበች፣ በዘመነኛ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች እና በታሪካዊ ኪነ ሕንጻዎች የተጌጠች ከተማ ናት። ከዚህ ባሻገር የአምራች ኢንዱስትሪዎች መናገሻም ናት። የምቹ ከተሜነትና ጠንካራ የስራ ባህል በግላጭ የሚስተዋልባት ከተማ። የዓለማችን ገዙፉ በጣም ሞቃታማ አየር ጸባይ ባላት ቻንግሻ ሌት ከቀን ይሰራል። ፋብሪካዎቿ አይተኙም። ሌትና ቀኑ የሚታወቀው በሰዓት ብቻ እንጂ የስራና የንግድ ድባቡ እኩል ነው። ብርሃናማዋ ቻንግሻ ‘የቻይዊያን መስቀል’ በተሰኘው በቀይ በተቀለመው መስቀልም ትታወቃለች። በርግጥ ከዓለማችን ግዙፍ ማማዎች አንዱ የሆነው ሕንጻም መገኛ ናች። በጥቅሉ የቻይና ጉብኝት ትዝብቴ የገናና ታሪክ ባለቤቷ ሀገር ከባድ ውጣ ውረዶችን አልፋ ዛሬ ዓለምን እየቀደመች መሆኑን ሳስብ፤ እንደቻይና ሁሉ የሺ ዘመናት ገናና ታሪክና አኩሪ ገድል ያላት ኢትዮጵያስ የሚል ተጠየቅ እንዳውጠነጥን አድርጎኛል። ቻይናዊያን የዘመን የፈተና ቋጠሮዎቻቸውን ፈታተው ከዛሬ ከፍታ ሰገነት ላይ ወጥተዋል። ከዛሬም በበለጠ ነገን በጽኑ መሰረት ላይ እየገነቡ ነው። እኛስ? ብዬ ሳስብ በቁጭትና በተስፋ ተዋጥኩ! ሰላም!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም