ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በክልሉ የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭን ለመቅረፍ ምግብና ስርዓተ ምግብ ላይ ይሰራል
Jan 25, 2026 42
አዳማ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭ ችግሮችን ለመቅረፍ ለምግብና ስርዓተ ምግብ ትኩረት መሰጠቱን በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ ገለፁ። የኦሮሚያ ክልል የምግብና ስነ ምግብ ምክር ቤት በክልሉ የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭን ችግሮችን ለመቅረፍ እየተከናወኑ ባሉ ስራዎች ላይ የምምክር መድረክ በአዳማ አካሄዷል ። በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ እንደገለፁት በክልሉ የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭ ችግሮችን ለመቅረፍ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ።   በተለይም ችግሩን ለመቅረፍ ለምግብና ስርዓተ ምግብ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰዋል። የኦሮሚያ የምግብና ስነ ምግብ ምክር ቤትም እስከ ወረዳ ድረስ አደረጃጀት በማዋቀር በቀዳማይ ልጅነት ልማት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም ከጽንስ እስከ ስድስት ዓመት ዕድሜ ያሉ ሕጻናት በአዕምሮ እና በአካል እንዲበለጽጉ የማድረግ ዓላማን አንግቦ ተግባራዊ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ በዚህም በምግብና ስነ ምግብ እጥረት የሚከሰቱ የመቀንጨርና የመቀጨጭ ችግሮችን ለመቀነስ በእናቶች፣ በቤተሰብ ምጣኔ፣ በግብርና፣ በትምህርትና በኢኮኖሚያዊ መስኮች ላይ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። መድረኩም በክልሉ የምግብና ስርዓተ ምግብ ችግሮችን ለመቅረፍ የተሰሩ ስራዎችን በአግባቡ በመፈተሽ በቀጣይ የተቀናጀ ጥረት ለማድረግ መሆኑንም አስገንዝበዋል ።   በሰቆጣ ቃልኪዳን የሞዴል ወረዳዎች ኢንሼቲቪ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ እስራኤል ሃይሉ በመድረኩ ላይ ባቀረቡት ጽሁፍ እንዳመለከቱት የሰቆጣ ቃልኪዳን በሁሉም ክልሎች ከ500 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭ ችግሮችን ለመቅረፍ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የህፃናትን መቀንጨር ዜሮ ለማድረግ በተጀመሩ ስራዎች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ጠቁመዋል ። ለዚህም በመደኛነት እየተከናወኑ ካሉት ስራዎች መካከል በምግብና ስርዓተ ምግብ ውጤታማ ለማድረግ በወተት፣ በማር፣ በዶሮ፣ ዓሣ ልማት ላይ መሰራቱን አንስተዋል።    
በክልሉ የጤና ተቋማትን አገልግሎት አስጣጥ ለማሳደግ ለህብረተሰብ ተሳትፎ ትኩረት ተሰጥቷል
Jan 25, 2026 36
አዳማ ፤ጥር 17/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል የጤና ተቋማትን አገልግሎት አስጣጥ ለማሳደግ ለህብረተሰብ ተሳትፎ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ቡድን በምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሰትና ሉሜ ወረዳዎች በመገኘት በጤና አገልግሎት በተሰሩ ሞዴል ስራዎች ላይ የልምድ ልውውጥ አድርጓል። የኦሮሚያ ጤና ቢሮ አማካሪ አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ለኢዜአ እንዳሳታወቁት በክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራት፣ ፍትሃዊነትና ደህንነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው። ለስኬቱም የጤና ተቋማትን በግብአትና በሰው ሀይል ለማሟላትና ጽዱ ለማድረግ ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።   የጤና ተቋማቱን አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመንና የመድሀኒት አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ የማህበረሰብ መድሀኒት ቤቶች በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ መገንባታቸውን አመልክተዋል። የማህበረሰቡን የጤና ዋስትና ለማረጋገጥም በአነስተኛ ክፍያ ዓመቱን ሙሉ የህክምና አገልግሎት ማግኘት እንዲችል የጤና መድህን አገልግሎት ማስፋፋት መቻሉንም ጠቅሰዋል። በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች አማካኝነትም ቤት ለቤት ትምህርት በመስጠት ህብረተሰቡ ከተላላፊና ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች እራሱን እንዲከላከል እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የምስራቅ ሸዋ ዞን ጤና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን አብሬ በበኩላቸው በዞኑ ጠንካራ የጤና አገልግሎትን ለመገንባት ከህበረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በተሰራው ስራም የዞኑ ሆስፒታሎች፣ ጤና ጣቢያዎችና ጤና ኬላዎች ሞዴል ሆነው እንዲወጡ መሰራቱን ተናግረዋል። በሆስፒታል ደረጃ ሲሰጡ የነበሩ አልትራሳውንድ የመሳሰሉ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችን በ46 ጤና ጣቢያዎች በሟሟላት ህብረተሰቡን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ጠቅሰዋል። የጤና አገልግሎት መረጃን ዲጂታላይዝድ ማድረግና ተቋማቱን በማስዋብ ለተገልጋይና ለባለሙያዎች ምቹ ማድረግ ላይ መሰራቱን ገልፀዋል ። በምስራቅ ሸዋ ዞን የቦሰት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጉተማ ቢፍቱ የዲጂታል ጤና ቴክኖሎጂ ሥርዓትን ከማጠናከር እንዲሁም ህክምና አገልግሎትን ከማዘምን ረገድ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በተለይ በህክምና ተቋማት የሚስተዋሉ የህክምና ግብዓቶችን ከሟሟላት ባለፈ ጤና ተቋማትን ለማስዋብ ከወረዳው በጀት መመደቡን ጠቅሰው ጤና ተቋማትም የውሰጥ ገቢያቸውን እንዲጠቀሙ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል። የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጤና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ፉአድ ጁአድ በሰጡት አስተያየት በቦሰት ወረዳ እና ወለንጪቲ ከተማ የሚገኙ ሞዴል ጤና ጣቢያና ጤና ኬላ አገልግሎት አሰጣጡ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል ። በህክምና ተቋማቱ በተደረገው ሪፎርም የጤና ተቋማት በዘመናዊ መሳሪያዎችና በሰው ሃይል በሚገባ መደራጀታቸውን፣ ለተገልጋይና ለባለሙያዎች ምቹና ማራኪ መደረጉን መመልከታቸውን ጠቅሰዋል። በልምድ ልውውጡ ያገኙትን ተሞክሮ ወደ ዞኑ ጤና ተቋማት ወስደው በተግባር ለማዋል እንደሚሰሩ አመላክተዋል።        
በክልሉ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በማቋቋም ህዝቡን በልማት እንዲክሱ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jan 25, 2026 60
ጎንደር ፤ጥር 17/2018 (ኢዜአ) ፡-በአማራ ክልል የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በአጭር ጊዜ በማቋቋም ህዝቡን በልማት እንዲክሱ የሚደረጉ ቅንጅታዊ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ። በብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን አስተባባሪነት በጠዳ የስልጠና ማእከል የተሀድሶ ስልጠና ሲከታተሉ ለቆዩ የቀድሞ ታጣቂዎች የሽኝትና የምረቃ ስነ ስርአት ዛሬ ተከናውኗል። በስነ ስርአቱ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ በሪሁን መንግስቴ እንደተናገሩት የዘላቂ ሠላም ስምምነቱ ክልሉን ወደ ተሟላ ሠላም ለማሸጋገር ምቹ መደላድል ፈጥሯል።   በሠላም ስምምነቱ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች የሠላም አማራጭን በመከተል መግባታቸውን ጠቁመው የተሀድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ የማቀላቀል ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የክልሉ መንግስት የቀድሞ ታጣቂዎች በመረጡት የስራ መስክ ተሰማርተው እራሳቸውን ማቋቋም እንዲችሉና ህብረተሰቡን በልማት እንዲክሱ የስራ እድሎችን ከማመቻቸት ጀምሮ የሙያ ስልጠና እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። የሠላም ስምምነቱን ተከትሎ የገቡ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋሞ ተግባራት እየተከናወነ ነው ያሉት ደግሞ በብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን የዲሞብላይዜሽን ዳይሬክተር ኮሎኔል ጎሳዬ ጥላሁን ናቸው።   ብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽኑ በአማራና በትግራይና ክልሎች በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ 502ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል መካሻ ጀንበሬ በአማራ ክልል ዘላቂ ሠላም ለማረጋገጥ በተደረገው ጥረት የሰላም አማራጭ ተቀብለው ለመጡ የቀድሞ ታጣቂዎች ምስጋና አቅርበዋል።   የህዝብን ሰላም በማስቀደም ፣ቀጠናዊ ጉዳዮችን በመገምገምና የህዝቡን ስሜት በመረዳት ከመንግስት ጋር የሰላም ስምምነት ላይ መድረሱን የተናገሩት ደግሞ የታጣቂ ቡድኑ የቀድሞ አመራር የነበሩት ረዳት ፕሮፌሰር እያሱ አባተ ናቸው። የክልሉን ሠላም ለማናጋትና በህዝብ ላይ በደል የማድረስ ተልእኮ ያላቸው ቡድኖችን እንዲሁም የታሪካዊ ጠላቶችን ሴራ ለማምከን ከመንግስት ጋር ተባብረው ለመስራት እንዳቀዱም ተናግረዋል።   የተሀድሶ ስልጠናውን ከተከታተሉ የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል አስር አለቃ አዳነ መሳፍንት በበኩላቸው የክልሉን ህዝብ ወደ ግጭት በማስገባት የበደሉትን ህዝብ በልማት ለመካስ መወሰናቸውን ተናግረዋል። በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት የበደሉትን ህዝብ በልማት ለመካስ መዘጋጀታቸውን ያስረዱት ሌላው የቀድሞ ታጣቂ ቶማስ አያሌው ናቸው። አሁን ላይ ከጥፋታቸው ተምረው መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ በመከተል ወደ መደበኛ ስራቸው ለመመለስ የተሀድሶ ስልጠና መውሰዳቸውን አንስተው ሌሎች በተሳሳተ መንገድ ጫካ የቀሩ ወገኖችም እድሉን እንዲጠቀሙ መክረዋል። በስነ ስርእቱ ላይ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።        
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ  ብቃት ያለው የሰው ሃይል የማፍራትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል
Jan 25, 2026 61
አዲስ አበባ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ብቃት ያለው የሰው ሃይል የማፍራትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ዛሬ የክልሉ መንግስት በ60 ሚሊየን ብር ወጪ ያስገነባው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በፕሮፌሰር ገቢሳ እጄታ እናት ስም ተመርቆ ለማህበረሰቡ አገልግሎት ክፍት ሆኗል።   የቢሮ ኃላፊው ቶላ በሪሶ(ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ብቃት ያለው የሰው ሃይል የማፍራትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል። በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ቡኡራ ቦሩ በተሰኙ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ለመማር ማስተማር ስራው መሰረታዊው ጉዳይ የትምህርት ቤቶች ደረጃን የማሻሻሉ ተግባርም መሆኑንም ገልጸዋል።   ትውልዱ በእውቀት ተመራምሮ ለሀገሩና ለዓለም ውጤት ለማስገኘት ጠንክሮ መማር እንዳለበት የገለጹት ደግሞ ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጄታ ናቸው። የተገነባው ትምህርት ቤት ለዚሁ አጋዥ መሆኑና በእናታቸው ስም መሰየሙ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል። በቀጣይም ትምህርት ቤቱን ይበልጥ በቴክኖሎጂ በማደራጀት የምርምርና የልህቀት ማዕከል ሆኖ እንዲቀጥል ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር እንደሚሰሩም ፕሮፌሰሩ ጠቁመዋል።   የምዕራብ ሸዋ ዞን ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ባንዲራ ጋላና፣ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን የመገንባትና ያሉትን የማስፋፋት ስራዎች በሰፊው እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የትምህርት ቤቱ መገንባት በአካባቢው የነበረውን የትምህርት ቤቶች እጥረት በመቅረፍ ጥራት ያለው ትምህርት ለመስጠት ያስችላል ሲሉም አስረድተዋል። ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤትም የተማሪዎች መማሪያ ክፍል፣ የአስተዳደር ሕንፃና ሌሎች አገልግሎት መስጫዎችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።   በምረቃው ላይ የተገኙት የአካባቢው ነዋሪዎችም ኦሎንኮሚ ሞቱ አያኖ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአካባቢያቸው ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ልጆቻቸው ጥራት ያለው ትምህርት በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል። ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ትምህርት ቤት በክልሉ ምዕራብ ሸዋ ዞን ኤጄርሳ ላፎ ወረዳ ሲሆን መታሰቢያነቱም ለእናታቸው ወይዘሮ ሞቱ አያኖ መሆኑ ታውቋል።
የሌማት ትሩፋትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ለማር ምርታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው
Jan 25, 2026 61
አዲስ አበባ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦የሌማት ትሩፋትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ለማር ምርታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር ገለፀ። የኢትዮጵያ ምቹ የአየር ጠባይና የአረንጓዴ አሻራ የደን ሽፋን ዕድገት የበርካታ ዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል። በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ አማካሪ ግርማ ሙሉጌታ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የግብርና ምርታማነትን ማሻሻል መርሃ ግብሮች በማር ምርታማነት ላይ እመርታዊ ውጤት እያስገኘ ነው። በተለይም የሌማት ትሩፋትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች የዜጎችን የንብ ማነብ ተነሳሽነት በማሳደግ በማር ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ውጤት አንዲመዘገብ እያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ የማር ምርታማነትም ዜጎች የተመጣጠነ የምግብ ሥርዓት የሚያገኙበትን አማራጭ በመፍጠር የውጭ ምንዛሬ ገቢ ጭምር እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም የዜጎችን የንብ ማነብ የሥራ ባህል በማሳደግ የማር ምርታማነትን ማሻሻል የሚያስችል ምኅዳር የመፍጠር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አንስተዋል። በማር ምርታማነት ለተመዘገበው ስኬትም የንብ አናቢዎች ዘመናዊ የአመራርት ዘዴ የግንዛቤ ማስጨበጫና የግብዓት አቅርቦት መሻሻል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚህም ባለፈው በጀት ዓመት 326ሺህ ሜትሪክ ቶን የማር ምርት በመሰብሰብ በተያዘው በጀት ዓመት 375 ሺህ ሜትሪክ ቶን የማር ምርት ለመሰብሰብ በተያዘው ዕቅድ መሠረት አበረታች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። የማር ምርት በጥራትና በብዛት በማምረት የውጭ ገበያ የማር ምርት አቅምን ለማሳደግ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።   የኢትዮጵያ ንብ ሃብት ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ነጋሽ በቃና በበኩላቸው፤ መንግስት ለግብርና ምርታማነት የሰጠው ትኩረት በማር ምርታማነት ላይ ውጤት እንዲገኝ እያስቻለ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራና የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሮችም በርካታ ዜጎች በንብ ማነብ የሥራ መስክ በመሰማራት የማር ምርታማነት ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የድርሻውን እንዲወጣ እያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።    
የሚታይ
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የራስን ተፈጥሯዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ-ምድራዊና ታሪካዊ ሃብት ምላሽ የማስገኘት ምክንያታዊ የሕልውና ጉዳይ ነው
Jan 25, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የራስን ተፈጥሯዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ-ምድራዊና ታሪካዊ ሃብት ምላሽ የማስገኘት ምክንያታዊ የሕልውና ጉዳይ መሆኑን ምሁራነ ገለጹ። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቂያና የጋራ ትርክት መገንቢያ መሆኑንም የተናገሩት። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ-ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ የህልውና ጥያቄ መሆኑ ይታወቃል። በኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራንም፤ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን እንድታጣ የተደረገችበት ታሪካዊ ሴራ የሚያስቆጭ መሆኑንም ገልጸዋል።   የባህልና ታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አህመድ ዘካርያ፤ የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ማንነትና ስልጣኔ ከቀይ ባሕር ባለቤትነት ጋር በእጅጉ ጥብቅ ቁርኝት አለው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም የራስን ተፈጥሯዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ-ምድራዊና ታሪካዊ ሃብት ምላሽ የማስገኘት ምክንያታዊ የሕልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ምላሽ የማስገኘት ቀጣናዊና አሕጉራዊ ሰላምና ደኅንነትን በማስጠበቅ ለፍትሐዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ዕድገት መሠረት እንደሚሆን ተናግረዋል። ኢትዮጵያውያንም የሀገራቸውን ሉዓላዊነት፣ ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስከብሩ ጽኑ ህዝቦች መሆናቸውን የዓድዋ ድል ሕያው ምስክር መሆኑን አስታውሰዋል። የጋራ ተግባቦት ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ዓይነተኛ ሚና አለው ያሉት ምሁሩ፤ አሰባሳቢ ትርክት ግንባታም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። በዚህም የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ለማስገኘት በሚደረገው ጥረት ሁሉም ዜጋ በከፍተኛ የኃላፊነት መንፈስ በመተባበር ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር መስራት እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። በአሁኑ ወቅትም የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ምላሽ ለማስገኘት የሚደረገው ጥረት የሀገርን ዕድገትና ቀጣዩን ትውልድ ታሳቢ ያደረገ ወሳኝ ብሔራዊ አጀንዳ መሆኑንም አስረድተዋል።   በውጪ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ተመራማሪ ጋሻው አይፈራም(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ታሪክና ስልጣኔ ከባሕር በር ባለቤትነት ጋር የተሰናሰለ ነው ብለዋል። ለአብነትም ከአክሱም ዘመነ መንግሥታት ጀምሮ ለበርካታ ሺህ ዘመናት ያህል ቀይ ባሕር የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ወሰንና የግዛት መዳረሻ አካል ሆኖ እንደቆየ አስታውሰዋል። በታሪካዊ ጠላቶች ሴራ እና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በቅጡ ባልተገነዘቡ ውስን ቡድኖች አማካኝነት ኢትዮጵያ ከተፈጥሯዊ የባሕር በር ወሰኗ እንድትገለል መደረጉን አስታውሰዋል። በዚህም የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሕጋዊ፣ ሥነ-ልቦናዊ፣ መልክዓ-ምድራዊ እና ፍትሕዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ትክክለኛና ምክንያታዊ ጥያቄ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ ለሰላም ግንባታ እና ለልማት ስራዎች የተሰጠው ትኩረት፣ ለቱሪዝም ዘርፉ እድገትና ማንሰራራት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jan 25, 2026 67
ባህር ዳር፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ለሰላም ግንባታ እና ለልማት ስራዎች የተሰጠው ትኩረት፣ ለቱሪዝም ዘርፉ እድገትና ማንሰራራት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ገለጸ። በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት በክልሉ ከዘርፉ ከ7 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ መገኘቱንም አስታውቋል። በኢትዮጵያ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራባቸው ከሚገኙትና ከአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች መካከል ቱሪዝም አንዱ ነው። የመደመር መንግስት በኢትዮጵያ ያለውን የቱሪዝም ሀብት በአግባቡ መለየት፣ ማልማትና መጠቀም ላይ ያሉ ክፍተቶችን ለመሙላት በገበታ ፕሮጀክቶች የተገበራቸው የቱሪዝም ልማቶች በዘርፉ ዕድገት ላይ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል። የአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ መልካሙ ጸጋዬ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ በክልሉ በመጣው የተረጋጋ ሰላም በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎች የቱሪዝም መስህቦችን ለመጎብኘት እንዲመጡ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። በክልሉ ሃይማኖታዊና ታሪካዊ የአደባባይ በዓላት ያለምንም የጸጥታ ችግር መከበራቸውን ጠቅሰው፣ ተቀዛቅዞ የቆየው የቱሪዝም ዘርፍ በእነዚህ በዓላት መነቃቃቱን አመልክተዋል። በመሆኑም በክልሉ ለሰላም ግንባታና ለልማት ስራዎች የተሰጠው ትኩረት፣ ለቱሪዝም ዘርፉ እድገትና ማንሰራራት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት 10 ነጥብ 2 ሚሊየን ቱሪስቶች የክልሉን የመስህብ ሥፍራዎች መጎብኘታቸውን አመልክተው፣ ከእነዚህ ውስጥ 24 ሺህ የሚሆኑት የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች መሆናቸውን አስታውቀዋል። በዚህም የጥምቀት በዓልን ሳያካትት ከ7 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን አንስተዋል። በክልሉ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት፣ የፋሲል አብያተ መንግስታት ጥገና እና የሌሎች ቅርሶች ጥገና፣ ጥበቃና እንክብከቤ የቱሪስቶችን ቀልብ እየሳበ መምጣቱን አመልክተዋል። እንዲሁም ለጎብኚዎች እየተሰጠ ያለው ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት የቱሪስቶች የቆይታ ጊዜ ከፍ እንዲል ማድረጉን አብራርተዋል። ቀደም ሲል የነበረው አማካይ የቱሪስቶች የቆይታ ጊዜ ከሁለት እስከ ሦስት ቀናት እንደነበረ አንስተው፤ አሁን ላይ ወደ አምስት ቀናት ከፍ ማለቱን ገልጸዋል። በቀጣይም የተገኙ ውጤቶችን የበለጠ አጠናክሮ በማስቀጠል ክልሉ ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ሆኖ እንዲዘልቅ የ25 ዓመት የልማት ዕቅድና የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ መዘጋጀቱን አመልከተዋል።
የኢትዮጵያን ክብር አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ተኝተን አናድርም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jan 24, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን ክብር፣ አንድነት እና ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ተኝተን አናድርም ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ የጥቁር አንበሳ የአየር ላይ ትርኢት ተካሂዷል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኢትዮጵያን ለመድፈር ለሞከሩ ኃይሎች ሁነኛ መድሃኒት ሆኖ ሀገር ያጸና ተቋም ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ ማደግ ከቻለች የጸናች እና የተከበረች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንችላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባለፉት 90 ዓመታት በብዙ ከፍታና ዝቅታ ውስጥ አልፏል። ባለፉት አምስት ዓመታት የ85 ዓመቱን ስራችንን የሚተካከሉ የቴክኖሎጂ፣ የሰው ኃይል፣ አየር በአየር፣ አየር በምድር ብቻ ሳይሆን ከአየር ጥቃት ኢትዮጵያን ለመከላከል የሚያስችሉ አቅም መገንባቱን ጠቅሰዋል። በአየር ኃይል መብቃት፣ ማሳደግ የሚያስፈልግበት ዋናው ምክንያት በስጋና በአጥንት ድል ማስመዝገብ ያደረ፣ የቀረ ስርዓት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተኩስ አቅም፣ በቴክኖሎጂ ብዙ ምሽጎች ማፍረስና ውጊያን ማሳጠር ታሳቢ ያደረገ አቅጣጫ እንከተላለን ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አሁን ያለውን የአየር ኃይል አቅም በእጥፍ ደረጃ ለማሳደግ ግልጽ እቅድ፣ በጀት እና ምንጭ ለይቶ ከዋና ዋና አምራቾች ጋር በትብብር ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። በ2030 ወደ አምስተኛው ትውልድ የሚሸጋገር፣ በቁጥርም ከተዋጊም አኳያ አሁን ያለው በእጥፍ እንደሚያድግ ገልጸዋል። ጠላቶቻችን ከቅርብና ከሩቅ የኢትዮጵያን አጠቃላይ አቅም ለማዳከም፣ ስትራቴጂክ ጥቅሞቿን ለማደናቀፍና ጥቅሞቿን ለመጋራት በብዙ ደክመዋል፣ በብዙ ሰርተዋል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከወዳጆቿ ጋር በትብብር ለመስራት በሯ ክፍት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በትብብር አብሮ ለመስራት፣ አብሮ ለማደግ ያለንን ቁርጠኝነት አረጋግጣለሁ ብለዋል። የኢትዮጵያን ክብር፣ አንድነትና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ተኝተን የማናድር መሆኑን በድጋሚ አረጋግጣሉ ሲሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ካለችበት የታሪክና የሀብት ጥልቀት በተጨማሪ አሁን ላይ በዘመናዊ የጦር ቴክኖሎጂ ራሷን እያዘመነች መሆኑን ገልጸዋል። አሁንም በድሮው አስተሳሰብና ቴክኖሎጂ ላይ ለቀሩ አካላት የኢትዮጵያን እድገትና ወደፊት መራመድ በቅጡ ሊረዱት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከኢትዮጵያ ጋር ተስማምቶና ተባብሮ ማደግ ብቸኛው አዋጭ መንገድ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ ትናንትና ላይ የቆመች ሀገር አይደለችም ብለዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ሀገር በቀል የፍትሕ ሥርዓቶችን ማዘመን ለፍትሕ ተደራሽነትና ለሰላም ግንባታ ወሳኝ ነው
Jan 24, 2026 87
አዲስ አበባ፤ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፡- ሀገር በቀል የፍትሕ ሥርዓቶችን ማዘመን ለፍትሕ ተደራሽነትና ለሰላም ግንባታ ወሳኝ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋራ ትብብር የተዘጋጀው “የሕግ የበላይነትና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች - ለዘላቂ ሰላም እና ዕድገት” በሚል መሪ ሀሳብ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ በባህር ዳር በመካሄድ ላይ ነው።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶችና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም፣ ለዕድገትና ኢንቨስትመንት መሳለጥ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። እንደ ሽምግልና ያሉ ሀገር በቀል ሥርዓቶች በመግባባትና ማኅበረሰባዊ ሰላምን በመፍጠር ላይ የተመሠረቱ እንደሆኑ ጠቅሰው፤ ለውስብስብ ችግሮች ቅቡልነት ያለው መፍትሔ እንደሚያመጡም ጠቁመዋል። መደበኛው ፍርድ ቤት በውሳኔ አሰጣጥ ላይ እንደሚያተኩር በመጥቀስ፣ ባህላዊ የፍትሕ ስርዓቶች ግን እስከ ዘላቂ ዕርቅና ማኅበራዊ መስተጋብር ድረስ እንደሚዘልቁ አስረድተዋል። በሀገራችን ብሎም በአማራ ክልል የሚተገበሩ ሀገር በቀል የፍትሕ አሠራሮች በትክክል ጥቅም ላይ ከዋሉ በመደበኛ የፍትሕ ተቋማት ላይ ያለውን ከፍተኛ የሥራ ጫና ትርጉም ባለው መልኩ እንደሚያቃልሉና በማኅበረሰቡ ዘንድ የባለቤትነት ስሜት ያላቸው መፍትሔዎችን እንደሚያቀርቡም አስገንዝበዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአማራ ክልል የድህነት ፈተናዎች፣ ግጭቶች፣ ክርክሮች እና ያለመግባባቶች መደራረብ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶችን እንደፈተኗቸው አንስተዋል። በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ፣ በተለያዩ ፖለቲካዊ እና ግላዊ ምክንያቶች መሣሪያ ያነሡ አካላት፣ ባህላዊውንም ሆነ መደበኛውን የፍትሕ ሥርዓቱን ለማዳከም ሆን ብለው ሠርተዋል ነው ያሉት። በሀገር አቀፍ ደረጃ ተደራሽና በመርሕ ላይ የቆመ ፍትሕን ለማስፈን ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶችን ከዘመናዊ ዕሳቤዎችና ከሀገራዊ ሪፎርሙ ጋር ማጣጣም እንደሚገባ ጠቁመዋል። የሀገር በቀል ተቋማትን አሠራር በሕግ በመደገፍና በማዘመን ተቋማዊ ቁመና እንዲኖራቸው ማድረግ ወሳኝ መሆኑንም ጠቁመዋል።   በመደበኛና በባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶች መካከል በተናበበ መልኩ የሚሠራበትን ዐውድ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸው፤ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ባህላዊና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎችን በመደበኛው የፍትሕ ሥርዓት ውስጥ በቋሚነት ማዋቀር ወቅቱ የሚጠይቀው ግዴታ መሆኑን ጠቁመዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የግልግልና የዕርቅ ሥርዓት ሕግ እንዲሁም በአማራ ክልል የጸደቀው የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ ዐዋጅ ለፍትሕ ዘርፉ ተቋማዊና ዘመናዊ ቁመና ማጎናጸፋቸውን ገልጸዋል። አማራጭ የሙግትና የክርክር መፍቻ ሥርዓቶችን ማጠናከር በድኅረ-ግጭት ዐውድ ዕርቅ ለማስፈን፣ የተሰበሩ ግንኙነቶችን ለመጠገንና ውይይትን ከቅራኔ ለማስቀደም ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የመደመር መንግሥት የትላንት በጎ እሴቶችን ከዛሬ አዳዲስ እሴቶች ጋር በማጣመር ነገን የመገንባት ጽኑ እምነት አለው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የነገዋ የበለጸገች ኢትዮጵያ የባህላዊና የመደበኛ ፍትሕ ሥርዓቶች አዎንታዊ ጥምረት እንደሚያስፈልጋት አስረድተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በክልሉ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በማቋቋም ህዝቡን በልማት እንዲክሱ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jan 25, 2026 60
ጎንደር ፤ጥር 17/2018 (ኢዜአ) ፡-በአማራ ክልል የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በአጭር ጊዜ በማቋቋም ህዝቡን በልማት እንዲክሱ የሚደረጉ ቅንጅታዊ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ። በብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን አስተባባሪነት በጠዳ የስልጠና ማእከል የተሀድሶ ስልጠና ሲከታተሉ ለቆዩ የቀድሞ ታጣቂዎች የሽኝትና የምረቃ ስነ ስርአት ዛሬ ተከናውኗል። በስነ ስርአቱ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ በሪሁን መንግስቴ እንደተናገሩት የዘላቂ ሠላም ስምምነቱ ክልሉን ወደ ተሟላ ሠላም ለማሸጋገር ምቹ መደላድል ፈጥሯል።   በሠላም ስምምነቱ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች የሠላም አማራጭን በመከተል መግባታቸውን ጠቁመው የተሀድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ የማቀላቀል ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የክልሉ መንግስት የቀድሞ ታጣቂዎች በመረጡት የስራ መስክ ተሰማርተው እራሳቸውን ማቋቋም እንዲችሉና ህብረተሰቡን በልማት እንዲክሱ የስራ እድሎችን ከማመቻቸት ጀምሮ የሙያ ስልጠና እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። የሠላም ስምምነቱን ተከትሎ የገቡ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋሞ ተግባራት እየተከናወነ ነው ያሉት ደግሞ በብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን የዲሞብላይዜሽን ዳይሬክተር ኮሎኔል ጎሳዬ ጥላሁን ናቸው።   ብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽኑ በአማራና በትግራይና ክልሎች በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ 502ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል መካሻ ጀንበሬ በአማራ ክልል ዘላቂ ሠላም ለማረጋገጥ በተደረገው ጥረት የሰላም አማራጭ ተቀብለው ለመጡ የቀድሞ ታጣቂዎች ምስጋና አቅርበዋል።   የህዝብን ሰላም በማስቀደም ፣ቀጠናዊ ጉዳዮችን በመገምገምና የህዝቡን ስሜት በመረዳት ከመንግስት ጋር የሰላም ስምምነት ላይ መድረሱን የተናገሩት ደግሞ የታጣቂ ቡድኑ የቀድሞ አመራር የነበሩት ረዳት ፕሮፌሰር እያሱ አባተ ናቸው። የክልሉን ሠላም ለማናጋትና በህዝብ ላይ በደል የማድረስ ተልእኮ ያላቸው ቡድኖችን እንዲሁም የታሪካዊ ጠላቶችን ሴራ ለማምከን ከመንግስት ጋር ተባብረው ለመስራት እንዳቀዱም ተናግረዋል።   የተሀድሶ ስልጠናውን ከተከታተሉ የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል አስር አለቃ አዳነ መሳፍንት በበኩላቸው የክልሉን ህዝብ ወደ ግጭት በማስገባት የበደሉትን ህዝብ በልማት ለመካስ መወሰናቸውን ተናግረዋል። በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት የበደሉትን ህዝብ በልማት ለመካስ መዘጋጀታቸውን ያስረዱት ሌላው የቀድሞ ታጣቂ ቶማስ አያሌው ናቸው። አሁን ላይ ከጥፋታቸው ተምረው መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ በመከተል ወደ መደበኛ ስራቸው ለመመለስ የተሀድሶ ስልጠና መውሰዳቸውን አንስተው ሌሎች በተሳሳተ መንገድ ጫካ የቀሩ ወገኖችም እድሉን እንዲጠቀሙ መክረዋል። በስነ ስርእቱ ላይ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።        
በምርጫው በሃሳብና በፖሊሲ አማራጮች ላይ ተከራክረን ሰላማዊ ፉክክር ለማድረግ ተዘጋጅተናል - የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jan 25, 2026 103
ቦንጋ፣ ጥር 17/2018 (ኢዜአ)፦ በመጪው ሀገራዊ ምርጫ በሃሳብና በፖሊሲ አማራጮች ላይ ተከራክረው ሰላማዊ ፉክክር ለማድረግ መዘጋጀታቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ መስጫ ቀን ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሂድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ከዚህም በመነሳት የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው የህዝብን ድምጽ ለማግኘት ከወዲሁ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆናቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ኢዜአ የምርጫ ዝግጅታቸውን በተመለከተ የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችን አነጋግሯል። ከፓርቲዎቹ አመራሮች መካከል የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ(ኢብአፓ) ሰብሳቢ መቅደስ መኮንን፤ ፓርቲያቸው ለሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት አባሎቹንና ደጋፊዎችን በማንቃት ለፉክክሩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በምርጫው ሀሳብ ይዞ በመቅረብና በፖሊሲ አማራጮች ላይ ክርክርና ፉክክር በማድረግ የህዝብ ይሁንታ ማግኘት የሚያስችል ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) ፓርቲ አመራርና የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ፀሐፊ ሰለሞን መኮንን እንዳሉት፤ ፓርቲያቸው ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ በቂ ዝግጅት እያደረገ ነው። ለምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት አባላትና ደጋፊዎቹ የሚጠበቅባቸውን ግዴታና ሃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በጋራ ምክር ቤቱ የሚገኙ ሁሉም ፓርቲዎች ለምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የበኩላቸውን ለመወጣት እየሰሩ መሆኑንም ጠቅሰዋል።   የካፋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ህብረት(ካህዴህ) ፓርቲ ሰብሳቢ ቦጋለ ኃይሌ በበኩላቸው ፓርቲያቸው የተሻለ ሀሳብና የፖሊሲ አማራጭ በመያዝ በምርጫው ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በዚህ በኩል ፓርቲያቸው ለአባላቱ የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀት ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ክብር አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ተኝተን አናድርም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jan 24, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን ክብር፣ አንድነት እና ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ተኝተን አናድርም ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ የጥቁር አንበሳ የአየር ላይ ትርኢት ተካሂዷል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኢትዮጵያን ለመድፈር ለሞከሩ ኃይሎች ሁነኛ መድሃኒት ሆኖ ሀገር ያጸና ተቋም ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ ማደግ ከቻለች የጸናች እና የተከበረች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንችላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባለፉት 90 ዓመታት በብዙ ከፍታና ዝቅታ ውስጥ አልፏል። ባለፉት አምስት ዓመታት የ85 ዓመቱን ስራችንን የሚተካከሉ የቴክኖሎጂ፣ የሰው ኃይል፣ አየር በአየር፣ አየር በምድር ብቻ ሳይሆን ከአየር ጥቃት ኢትዮጵያን ለመከላከል የሚያስችሉ አቅም መገንባቱን ጠቅሰዋል። በአየር ኃይል መብቃት፣ ማሳደግ የሚያስፈልግበት ዋናው ምክንያት በስጋና በአጥንት ድል ማስመዝገብ ያደረ፣ የቀረ ስርዓት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተኩስ አቅም፣ በቴክኖሎጂ ብዙ ምሽጎች ማፍረስና ውጊያን ማሳጠር ታሳቢ ያደረገ አቅጣጫ እንከተላለን ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አሁን ያለውን የአየር ኃይል አቅም በእጥፍ ደረጃ ለማሳደግ ግልጽ እቅድ፣ በጀት እና ምንጭ ለይቶ ከዋና ዋና አምራቾች ጋር በትብብር ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። በ2030 ወደ አምስተኛው ትውልድ የሚሸጋገር፣ በቁጥርም ከተዋጊም አኳያ አሁን ያለው በእጥፍ እንደሚያድግ ገልጸዋል። ጠላቶቻችን ከቅርብና ከሩቅ የኢትዮጵያን አጠቃላይ አቅም ለማዳከም፣ ስትራቴጂክ ጥቅሞቿን ለማደናቀፍና ጥቅሞቿን ለመጋራት በብዙ ደክመዋል፣ በብዙ ሰርተዋል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከወዳጆቿ ጋር በትብብር ለመስራት በሯ ክፍት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በትብብር አብሮ ለመስራት፣ አብሮ ለማደግ ያለንን ቁርጠኝነት አረጋግጣለሁ ብለዋል። የኢትዮጵያን ክብር፣ አንድነትና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ተኝተን የማናድር መሆኑን በድጋሚ አረጋግጣሉ ሲሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ካለችበት የታሪክና የሀብት ጥልቀት በተጨማሪ አሁን ላይ በዘመናዊ የጦር ቴክኖሎጂ ራሷን እያዘመነች መሆኑን ገልጸዋል። አሁንም በድሮው አስተሳሰብና ቴክኖሎጂ ላይ ለቀሩ አካላት የኢትዮጵያን እድገትና ወደፊት መራመድ በቅጡ ሊረዱት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከኢትዮጵያ ጋር ተስማምቶና ተባብሮ ማደግ ብቸኛው አዋጭ መንገድ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ ትናንትና ላይ የቆመች ሀገር አይደለችም ብለዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ሀገር በቀል የፍትሕ ሥርዓቶችን ማዘመን ለፍትሕ ተደራሽነትና ለሰላም ግንባታ ወሳኝ ነው
Jan 24, 2026 87
አዲስ አበባ፤ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፡- ሀገር በቀል የፍትሕ ሥርዓቶችን ማዘመን ለፍትሕ ተደራሽነትና ለሰላም ግንባታ ወሳኝ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋራ ትብብር የተዘጋጀው “የሕግ የበላይነትና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች - ለዘላቂ ሰላም እና ዕድገት” በሚል መሪ ሀሳብ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ በባህር ዳር በመካሄድ ላይ ነው።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶችና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም፣ ለዕድገትና ኢንቨስትመንት መሳለጥ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። እንደ ሽምግልና ያሉ ሀገር በቀል ሥርዓቶች በመግባባትና ማኅበረሰባዊ ሰላምን በመፍጠር ላይ የተመሠረቱ እንደሆኑ ጠቅሰው፤ ለውስብስብ ችግሮች ቅቡልነት ያለው መፍትሔ እንደሚያመጡም ጠቁመዋል። መደበኛው ፍርድ ቤት በውሳኔ አሰጣጥ ላይ እንደሚያተኩር በመጥቀስ፣ ባህላዊ የፍትሕ ስርዓቶች ግን እስከ ዘላቂ ዕርቅና ማኅበራዊ መስተጋብር ድረስ እንደሚዘልቁ አስረድተዋል። በሀገራችን ብሎም በአማራ ክልል የሚተገበሩ ሀገር በቀል የፍትሕ አሠራሮች በትክክል ጥቅም ላይ ከዋሉ በመደበኛ የፍትሕ ተቋማት ላይ ያለውን ከፍተኛ የሥራ ጫና ትርጉም ባለው መልኩ እንደሚያቃልሉና በማኅበረሰቡ ዘንድ የባለቤትነት ስሜት ያላቸው መፍትሔዎችን እንደሚያቀርቡም አስገንዝበዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአማራ ክልል የድህነት ፈተናዎች፣ ግጭቶች፣ ክርክሮች እና ያለመግባባቶች መደራረብ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶችን እንደፈተኗቸው አንስተዋል። በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ፣ በተለያዩ ፖለቲካዊ እና ግላዊ ምክንያቶች መሣሪያ ያነሡ አካላት፣ ባህላዊውንም ሆነ መደበኛውን የፍትሕ ሥርዓቱን ለማዳከም ሆን ብለው ሠርተዋል ነው ያሉት። በሀገር አቀፍ ደረጃ ተደራሽና በመርሕ ላይ የቆመ ፍትሕን ለማስፈን ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶችን ከዘመናዊ ዕሳቤዎችና ከሀገራዊ ሪፎርሙ ጋር ማጣጣም እንደሚገባ ጠቁመዋል። የሀገር በቀል ተቋማትን አሠራር በሕግ በመደገፍና በማዘመን ተቋማዊ ቁመና እንዲኖራቸው ማድረግ ወሳኝ መሆኑንም ጠቁመዋል።   በመደበኛና በባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶች መካከል በተናበበ መልኩ የሚሠራበትን ዐውድ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸው፤ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ባህላዊና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎችን በመደበኛው የፍትሕ ሥርዓት ውስጥ በቋሚነት ማዋቀር ወቅቱ የሚጠይቀው ግዴታ መሆኑን ጠቁመዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የግልግልና የዕርቅ ሥርዓት ሕግ እንዲሁም በአማራ ክልል የጸደቀው የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ ዐዋጅ ለፍትሕ ዘርፉ ተቋማዊና ዘመናዊ ቁመና ማጎናጸፋቸውን ገልጸዋል። አማራጭ የሙግትና የክርክር መፍቻ ሥርዓቶችን ማጠናከር በድኅረ-ግጭት ዐውድ ዕርቅ ለማስፈን፣ የተሰበሩ ግንኙነቶችን ለመጠገንና ውይይትን ከቅራኔ ለማስቀደም ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የመደመር መንግሥት የትላንት በጎ እሴቶችን ከዛሬ አዳዲስ እሴቶች ጋር በማጣመር ነገን የመገንባት ጽኑ እምነት አለው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የነገዋ የበለጸገች ኢትዮጵያ የባህላዊና የመደበኛ ፍትሕ ሥርዓቶች አዎንታዊ ጥምረት እንደሚያስፈልጋት አስረድተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ ማደግ ከቻለች የጸናች እና የተከበረች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንችላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jan 24, 2026 101
አዲስ አበባ፤ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፦‎ኢትዮጵያ በሚዛን በሁሉም ዘርፍ ማደግ ከቻለች የጸናች እና የተከበረች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንችላለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ አመት ክብረ በዓል እየተከናወነ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በክበረ በዓሉ ላይ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90 ዓመት ቢሆንም ለረጅም ዓመታት በቂ እና ተከታታይ ግንባታ እንዳልተደረገለት ገልጸዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት 85 ዓመቱን የሚተካከል የኢትዮጵያ አየር ኃይል በቴክኖሎጂ፣በሰው ኃይል እና ኢትዮጵያን ከአየር ጥቃት መከላከል የሚያስችል ብቃት መገንባቱን አመልክተዋል። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አሁን ያለንበትን የአየር ኃይል አቅም በእጥፍ ለማሳደግ እቅድ ይዞ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ዛሬ የአራተኛውን ትውልድ የመዋጋት አቅም የገነባው አየር ኃይሉ እ.አ.አ በ2030 ወደ አምስተኛው ትውልድ እንዲሸጋገር ይሰራል ብለዋል። ኢትዮጵያ በወታደራዊ አቅም ብቻ የተሟላ እድገት ማምጣት እንደማትችል እና ሁሉን አቀፍ እድገት እንደሚያስፈልጋት ገልጸዋል። በኢኮኖሚ፣በዲፕሎማሲ፣ፖለቲካ እና ወታደራዊ በሚዛን ሁሉን ማሳደግ ስንችል የጸናች ፣ የተፈራች እና የተከበረች ኢትዮጵያን ለልጆቻችን ማስረከብ እንችላለን ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ከወዳጆቿ ጋር ለመስራት ሁሉም በሯ ክፍት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለጠላቶቻችን መንግስት የኢትዮጵያን ጥቅም፣አንድነት እና ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ አንተኛም ብለዋል። የኢትዮጵያ ብልጽግና እና እድገት የማረጋገጥ ጉዞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና ይህንን የሚያቆም የትኛውም ኃይል እንደሌለ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ትናንት ላይ ቆማ የቀረች ሀገር አይደለችም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ነገን የዋጀ አቅም መገንባቷን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሰላም፣አንድነት እና ብልጽግና በኢትዮጵያውያን የጋራ ትብብር እውን ይሆናል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለሁሉ የምትበቃ እና ለሁሉም የምትሆን ለማድረግ በትጋት እንደሚሰራ አመልክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በክልሉ የዳበሩ የግጭት መፍቻ ስርዓቶችን በአግባቡ መጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው-ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ
Jan 24, 2026 78
አዲስ አበባ፤ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የዳበሩ የግጭት መፍቻና የፍትሕ ስርዓቶችን በአግባቡ መጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ ገለጹ። በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትብብር “የሕግ የበላይነትና አማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴዎች - ለዘላቂ ሰላም እና ዕድገት” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ከትናንት በጎ ዕሴቶችን መውሰድ፤ዛሬ ጠቃሚ አዳዲስ ዕሴቶችን መገንባት፤ ነገ ኢትዮጵያ እንድትበለጽግ የሚያደርጓት ቁልፍ ተግባራት ናቸው-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በክልሉ የፍትሕ ተቋማትን ተምሳሌትና የልምድ ተሞክሮ መቅሰሚያ የሚያደርጉ ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎች እየተከናወኑ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በመድረኩ ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ እንደገለጹት፤ በክልሉ ያሉ የዳበሩ የግጭት መፍቻና የፍትሕ ሥርዓቶችን በአግባቡ መጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው ብለዋል። በኮንፍረንሱ የተነሱት የህግ የበላይነት፣ አማራጭ የልዩነት መፍቻ መንገዶች፣ የዘላቂ ሰላምና የዘላቂ ልማት አጀንዳዎች አንገብጋቢና ወቅታዊ ናቸው ብለዋል። በሀገራችን ከለውጡ ወዲህ ከአጀንዳዎች ሁሉ ከፍ ብሎ የመጣው የመልማትና ሁለንተናዊ የብልፅግና አጀንዳ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ኢትዮጵያን በታሪክ ከምትጠቀስባቸው የግጭትና የድህነት አዙሪት አላቅቆ የበለፀገችና ለሌሎች ምሳሌ የሆነች ሀገር ለመገንባት ከፍተኛ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ከፍተኛ የልማት አጀንዳ በተቀሰቀሰበት በዚህ ወቅት በንግግር ሊፈቱ የሚችሉ ጉዳዮችን በኃይል ለማስፈጸም የሚሞክሩ አካላት የህብረተሰቡን ሰላም የሚነሱና የመልማት ፍላጎት የሚገቱ ችግሮችን መፍጠራቸውን ተናግረዋል። ልማት ሰላም ይፈልጋል ያሉት ሚኒስትሩ፥ የለውጡ መንግሥት ስለ ሰላም የዕይታና የፖሊሲ ለውጥ በማድረግ ዘላቂ ሰላምን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት አካሄድን ቀዳሚ አማራጭ ማድረጉን ጠቅሰዋል። የማንግባባባቸው ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራዊ ምክክርና የሽግግር ፍትሕ መዘርጋቱን አንስተው፥ መንግሥት ሁልጊዜም ችግሮች በሰላማዊ መንገድ በውይይት እንዲፈቱ ባለው ፅኑ አቋም ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪዎችን ማድረጉን አስረድተዋል። በአማራ ክልል የሰላም አማራጭን መርጠው ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ የተመለሱ አካላት ለዘላቂ ሰላም ግንባታው ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና የልማት ሥራዎች መሳካት ትልቅ ሚና እንደሚኖረው አብራርተዋል። በመሆኑም የታሪክና የትውልድ ተጠያቂነትን ከሚያስከትል ጥፋት በመቆጠብ መንግሥት ለሰላም የሰጠውን ዕድል በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም በጎ ሚና መጫወት እንደሚገባም ተናግረዋል። ከሰባ በላይ አማራጭ ባህላዊ የግጭትና የችግር መፍቻ ስርዓቶች መኖራቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፥ በአማራ ክልልም ለባህላዊ ስርዓቶች የተሰጠው ትኩረት የሚበረታታ ነው ብለዋል። የዳበሩ የግጭት መፍቻና የፍትሔ ስርዓቶችን በአግባቡ መጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑንም ጠቅሰዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ከትናንት በጎ ዕሴቶችን መውሰድ፤ዛሬ ጠቃሚ አዳዲስ ዕሴቶችን መገንባት፤ ነገ ኢትዮጵያ እንድትበለጽግ የሚያደርጓት ቁልፍ ተግባራት ናቸው-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jan 24, 2026 93
አዲስ አበባ፤ጥር 16/2018(ኢዜአ)፦ከትናንት በጎ ዕሴቶችን መውሰድ፤ዛሬ ጠቃሚ አዳዲስ ዕሴቶችን መገንባት፤ ነገ ኢትዮጵያ እንድትበለጽግ የሚያደርጓት ቁልፍ ተግባራት ናቸው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዛሬ በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋራ ትብብር "የሕግ የበላይነትና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች - ለዘላቂ ሰላም እና ዕድገት" በሚል የተዘጋጀውን ዓለም አቀፍ ጉባኤን አስጀምረዋል።   በዚህ ወቅት፥ ኢትዮጵያ መደበኛ የፍርድ ተቋማቷን ብታዘምንም አብዛኛው ሕዝባችን ችግሩን የሚፈታበት ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓት ግን ተገቢው ቦታ ሳይሰጠው ቆይቷል ብለዋል፡፡ የባሕርዳር በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን አሟልቶ እየተጠናቀቀ ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አሁን ግን በሀገራችንም ሆነ በክልላችን ተደራሽ፣ ቅቡልነት ያለው እና በመርሕ ላይ የቆመ ፍትሕን ለማስፈን እንዲቻል መደበኛና ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶች ተጣጥመውና ተናብበው የሚጓዙበትን ዐውድ መፍጠር የግድ የሚልበት ወቅት ላይ እንገኛለን ነው ያሉት፡፡ ለዚህ ደግሞ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶቻችንን ከዘመናዊ ዕሳቤዎች ጋር ማስተሣሠር፣ በሕግ መደገፍ እና አሠራሮቻቸውን ማዘመን፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከምንተገብራቸው ሪፎርሞች ጋር አሠናስሎ ማዋወቀር ለነገ የማይባል ሥራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የጎደላቸውን ሞልተን በትክክል ከተጠቀምንባቸው፣ በጉዳዮች ብዛት በከፍተኛ ጫና ውስጥ የሚገኙ መደበኛ የፍትሕ ተቋሞቻችንን ትርጉም ባለው ደረጃ ያግዛሉ፤ በማኅበረሰቡ ዘንድ የተሻለ ተቀባይነት እና የባለቤትነት ስሜት የሚንጸባረቅባቸውን መፍትሔዎች ያቀርባሉ። ይህ ኮንፈረንስ ይሄንን አዎንታዊ ጥምረት ለመፍጠር የተሻለውን መንገድ እንደሚጠቁም እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ፖለቲካ
በክልሉ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በማቋቋም ህዝቡን በልማት እንዲክሱ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jan 25, 2026 60
ጎንደር ፤ጥር 17/2018 (ኢዜአ) ፡-በአማራ ክልል የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በአጭር ጊዜ በማቋቋም ህዝቡን በልማት እንዲክሱ የሚደረጉ ቅንጅታዊ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ። በብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን አስተባባሪነት በጠዳ የስልጠና ማእከል የተሀድሶ ስልጠና ሲከታተሉ ለቆዩ የቀድሞ ታጣቂዎች የሽኝትና የምረቃ ስነ ስርአት ዛሬ ተከናውኗል። በስነ ስርአቱ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ በሪሁን መንግስቴ እንደተናገሩት የዘላቂ ሠላም ስምምነቱ ክልሉን ወደ ተሟላ ሠላም ለማሸጋገር ምቹ መደላድል ፈጥሯል።   በሠላም ስምምነቱ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች የሠላም አማራጭን በመከተል መግባታቸውን ጠቁመው የተሀድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ የማቀላቀል ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የክልሉ መንግስት የቀድሞ ታጣቂዎች በመረጡት የስራ መስክ ተሰማርተው እራሳቸውን ማቋቋም እንዲችሉና ህብረተሰቡን በልማት እንዲክሱ የስራ እድሎችን ከማመቻቸት ጀምሮ የሙያ ስልጠና እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። የሠላም ስምምነቱን ተከትሎ የገቡ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋሞ ተግባራት እየተከናወነ ነው ያሉት ደግሞ በብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን የዲሞብላይዜሽን ዳይሬክተር ኮሎኔል ጎሳዬ ጥላሁን ናቸው።   ብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽኑ በአማራና በትግራይና ክልሎች በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ 502ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል መካሻ ጀንበሬ በአማራ ክልል ዘላቂ ሠላም ለማረጋገጥ በተደረገው ጥረት የሰላም አማራጭ ተቀብለው ለመጡ የቀድሞ ታጣቂዎች ምስጋና አቅርበዋል።   የህዝብን ሰላም በማስቀደም ፣ቀጠናዊ ጉዳዮችን በመገምገምና የህዝቡን ስሜት በመረዳት ከመንግስት ጋር የሰላም ስምምነት ላይ መድረሱን የተናገሩት ደግሞ የታጣቂ ቡድኑ የቀድሞ አመራር የነበሩት ረዳት ፕሮፌሰር እያሱ አባተ ናቸው። የክልሉን ሠላም ለማናጋትና በህዝብ ላይ በደል የማድረስ ተልእኮ ያላቸው ቡድኖችን እንዲሁም የታሪካዊ ጠላቶችን ሴራ ለማምከን ከመንግስት ጋር ተባብረው ለመስራት እንዳቀዱም ተናግረዋል።   የተሀድሶ ስልጠናውን ከተከታተሉ የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል አስር አለቃ አዳነ መሳፍንት በበኩላቸው የክልሉን ህዝብ ወደ ግጭት በማስገባት የበደሉትን ህዝብ በልማት ለመካስ መወሰናቸውን ተናግረዋል። በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት የበደሉትን ህዝብ በልማት ለመካስ መዘጋጀታቸውን ያስረዱት ሌላው የቀድሞ ታጣቂ ቶማስ አያሌው ናቸው። አሁን ላይ ከጥፋታቸው ተምረው መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ በመከተል ወደ መደበኛ ስራቸው ለመመለስ የተሀድሶ ስልጠና መውሰዳቸውን አንስተው ሌሎች በተሳሳተ መንገድ ጫካ የቀሩ ወገኖችም እድሉን እንዲጠቀሙ መክረዋል። በስነ ስርእቱ ላይ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።        
በምርጫው በሃሳብና በፖሊሲ አማራጮች ላይ ተከራክረን ሰላማዊ ፉክክር ለማድረግ ተዘጋጅተናል - የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jan 25, 2026 103
ቦንጋ፣ ጥር 17/2018 (ኢዜአ)፦ በመጪው ሀገራዊ ምርጫ በሃሳብና በፖሊሲ አማራጮች ላይ ተከራክረው ሰላማዊ ፉክክር ለማድረግ መዘጋጀታቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ መስጫ ቀን ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሂድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ከዚህም በመነሳት የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው የህዝብን ድምጽ ለማግኘት ከወዲሁ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆናቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ኢዜአ የምርጫ ዝግጅታቸውን በተመለከተ የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችን አነጋግሯል። ከፓርቲዎቹ አመራሮች መካከል የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ(ኢብአፓ) ሰብሳቢ መቅደስ መኮንን፤ ፓርቲያቸው ለሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት አባሎቹንና ደጋፊዎችን በማንቃት ለፉክክሩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በምርጫው ሀሳብ ይዞ በመቅረብና በፖሊሲ አማራጮች ላይ ክርክርና ፉክክር በማድረግ የህዝብ ይሁንታ ማግኘት የሚያስችል ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) ፓርቲ አመራርና የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ፀሐፊ ሰለሞን መኮንን እንዳሉት፤ ፓርቲያቸው ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ በቂ ዝግጅት እያደረገ ነው። ለምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት አባላትና ደጋፊዎቹ የሚጠበቅባቸውን ግዴታና ሃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በጋራ ምክር ቤቱ የሚገኙ ሁሉም ፓርቲዎች ለምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የበኩላቸውን ለመወጣት እየሰሩ መሆኑንም ጠቅሰዋል።   የካፋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ህብረት(ካህዴህ) ፓርቲ ሰብሳቢ ቦጋለ ኃይሌ በበኩላቸው ፓርቲያቸው የተሻለ ሀሳብና የፖሊሲ አማራጭ በመያዝ በምርጫው ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በዚህ በኩል ፓርቲያቸው ለአባላቱ የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀት ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ክብር አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ተኝተን አናድርም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jan 24, 2026 113
አዲስ አበባ፤ ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን ክብር፣ አንድነት እና ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ተኝተን አናድርም ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ የጥቁር አንበሳ የአየር ላይ ትርኢት ተካሂዷል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኢትዮጵያን ለመድፈር ለሞከሩ ኃይሎች ሁነኛ መድሃኒት ሆኖ ሀገር ያጸና ተቋም ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ ማደግ ከቻለች የጸናች እና የተከበረች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንችላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባለፉት 90 ዓመታት በብዙ ከፍታና ዝቅታ ውስጥ አልፏል። ባለፉት አምስት ዓመታት የ85 ዓመቱን ስራችንን የሚተካከሉ የቴክኖሎጂ፣ የሰው ኃይል፣ አየር በአየር፣ አየር በምድር ብቻ ሳይሆን ከአየር ጥቃት ኢትዮጵያን ለመከላከል የሚያስችሉ አቅም መገንባቱን ጠቅሰዋል። በአየር ኃይል መብቃት፣ ማሳደግ የሚያስፈልግበት ዋናው ምክንያት በስጋና በአጥንት ድል ማስመዝገብ ያደረ፣ የቀረ ስርዓት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተኩስ አቅም፣ በቴክኖሎጂ ብዙ ምሽጎች ማፍረስና ውጊያን ማሳጠር ታሳቢ ያደረገ አቅጣጫ እንከተላለን ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አሁን ያለውን የአየር ኃይል አቅም በእጥፍ ደረጃ ለማሳደግ ግልጽ እቅድ፣ በጀት እና ምንጭ ለይቶ ከዋና ዋና አምራቾች ጋር በትብብር ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። በ2030 ወደ አምስተኛው ትውልድ የሚሸጋገር፣ በቁጥርም ከተዋጊም አኳያ አሁን ያለው በእጥፍ እንደሚያድግ ገልጸዋል። ጠላቶቻችን ከቅርብና ከሩቅ የኢትዮጵያን አጠቃላይ አቅም ለማዳከም፣ ስትራቴጂክ ጥቅሞቿን ለማደናቀፍና ጥቅሞቿን ለመጋራት በብዙ ደክመዋል፣ በብዙ ሰርተዋል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከወዳጆቿ ጋር በትብብር ለመስራት በሯ ክፍት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በትብብር አብሮ ለመስራት፣ አብሮ ለማደግ ያለንን ቁርጠኝነት አረጋግጣለሁ ብለዋል። የኢትዮጵያን ክብር፣ አንድነትና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ተኝተን የማናድር መሆኑን በድጋሚ አረጋግጣሉ ሲሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ካለችበት የታሪክና የሀብት ጥልቀት በተጨማሪ አሁን ላይ በዘመናዊ የጦር ቴክኖሎጂ ራሷን እያዘመነች መሆኑን ገልጸዋል። አሁንም በድሮው አስተሳሰብና ቴክኖሎጂ ላይ ለቀሩ አካላት የኢትዮጵያን እድገትና ወደፊት መራመድ በቅጡ ሊረዱት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከኢትዮጵያ ጋር ተስማምቶና ተባብሮ ማደግ ብቸኛው አዋጭ መንገድ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ ትናንትና ላይ የቆመች ሀገር አይደለችም ብለዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ሀገር በቀል የፍትሕ ሥርዓቶችን ማዘመን ለፍትሕ ተደራሽነትና ለሰላም ግንባታ ወሳኝ ነው
Jan 24, 2026 87
አዲስ አበባ፤ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፡- ሀገር በቀል የፍትሕ ሥርዓቶችን ማዘመን ለፍትሕ ተደራሽነትና ለሰላም ግንባታ ወሳኝ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋራ ትብብር የተዘጋጀው “የሕግ የበላይነትና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች - ለዘላቂ ሰላም እና ዕድገት” በሚል መሪ ሀሳብ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ በባህር ዳር በመካሄድ ላይ ነው።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶችና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም፣ ለዕድገትና ኢንቨስትመንት መሳለጥ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። እንደ ሽምግልና ያሉ ሀገር በቀል ሥርዓቶች በመግባባትና ማኅበረሰባዊ ሰላምን በመፍጠር ላይ የተመሠረቱ እንደሆኑ ጠቅሰው፤ ለውስብስብ ችግሮች ቅቡልነት ያለው መፍትሔ እንደሚያመጡም ጠቁመዋል። መደበኛው ፍርድ ቤት በውሳኔ አሰጣጥ ላይ እንደሚያተኩር በመጥቀስ፣ ባህላዊ የፍትሕ ስርዓቶች ግን እስከ ዘላቂ ዕርቅና ማኅበራዊ መስተጋብር ድረስ እንደሚዘልቁ አስረድተዋል። በሀገራችን ብሎም በአማራ ክልል የሚተገበሩ ሀገር በቀል የፍትሕ አሠራሮች በትክክል ጥቅም ላይ ከዋሉ በመደበኛ የፍትሕ ተቋማት ላይ ያለውን ከፍተኛ የሥራ ጫና ትርጉም ባለው መልኩ እንደሚያቃልሉና በማኅበረሰቡ ዘንድ የባለቤትነት ስሜት ያላቸው መፍትሔዎችን እንደሚያቀርቡም አስገንዝበዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአማራ ክልል የድህነት ፈተናዎች፣ ግጭቶች፣ ክርክሮች እና ያለመግባባቶች መደራረብ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶችን እንደፈተኗቸው አንስተዋል። በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ፣ በተለያዩ ፖለቲካዊ እና ግላዊ ምክንያቶች መሣሪያ ያነሡ አካላት፣ ባህላዊውንም ሆነ መደበኛውን የፍትሕ ሥርዓቱን ለማዳከም ሆን ብለው ሠርተዋል ነው ያሉት። በሀገር አቀፍ ደረጃ ተደራሽና በመርሕ ላይ የቆመ ፍትሕን ለማስፈን ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶችን ከዘመናዊ ዕሳቤዎችና ከሀገራዊ ሪፎርሙ ጋር ማጣጣም እንደሚገባ ጠቁመዋል። የሀገር በቀል ተቋማትን አሠራር በሕግ በመደገፍና በማዘመን ተቋማዊ ቁመና እንዲኖራቸው ማድረግ ወሳኝ መሆኑንም ጠቁመዋል።   በመደበኛና በባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶች መካከል በተናበበ መልኩ የሚሠራበትን ዐውድ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸው፤ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ባህላዊና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎችን በመደበኛው የፍትሕ ሥርዓት ውስጥ በቋሚነት ማዋቀር ወቅቱ የሚጠይቀው ግዴታ መሆኑን ጠቁመዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የግልግልና የዕርቅ ሥርዓት ሕግ እንዲሁም በአማራ ክልል የጸደቀው የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ ዐዋጅ ለፍትሕ ዘርፉ ተቋማዊና ዘመናዊ ቁመና ማጎናጸፋቸውን ገልጸዋል። አማራጭ የሙግትና የክርክር መፍቻ ሥርዓቶችን ማጠናከር በድኅረ-ግጭት ዐውድ ዕርቅ ለማስፈን፣ የተሰበሩ ግንኙነቶችን ለመጠገንና ውይይትን ከቅራኔ ለማስቀደም ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የመደመር መንግሥት የትላንት በጎ እሴቶችን ከዛሬ አዳዲስ እሴቶች ጋር በማጣመር ነገን የመገንባት ጽኑ እምነት አለው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የነገዋ የበለጸገች ኢትዮጵያ የባህላዊና የመደበኛ ፍትሕ ሥርዓቶች አዎንታዊ ጥምረት እንደሚያስፈልጋት አስረድተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ ማደግ ከቻለች የጸናች እና የተከበረች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንችላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jan 24, 2026 101
አዲስ አበባ፤ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፦‎ኢትዮጵያ በሚዛን በሁሉም ዘርፍ ማደግ ከቻለች የጸናች እና የተከበረች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንችላለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ አመት ክብረ በዓል እየተከናወነ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በክበረ በዓሉ ላይ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90 ዓመት ቢሆንም ለረጅም ዓመታት በቂ እና ተከታታይ ግንባታ እንዳልተደረገለት ገልጸዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት 85 ዓመቱን የሚተካከል የኢትዮጵያ አየር ኃይል በቴክኖሎጂ፣በሰው ኃይል እና ኢትዮጵያን ከአየር ጥቃት መከላከል የሚያስችል ብቃት መገንባቱን አመልክተዋል። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አሁን ያለንበትን የአየር ኃይል አቅም በእጥፍ ለማሳደግ እቅድ ይዞ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ዛሬ የአራተኛውን ትውልድ የመዋጋት አቅም የገነባው አየር ኃይሉ እ.አ.አ በ2030 ወደ አምስተኛው ትውልድ እንዲሸጋገር ይሰራል ብለዋል። ኢትዮጵያ በወታደራዊ አቅም ብቻ የተሟላ እድገት ማምጣት እንደማትችል እና ሁሉን አቀፍ እድገት እንደሚያስፈልጋት ገልጸዋል። በኢኮኖሚ፣በዲፕሎማሲ፣ፖለቲካ እና ወታደራዊ በሚዛን ሁሉን ማሳደግ ስንችል የጸናች ፣ የተፈራች እና የተከበረች ኢትዮጵያን ለልጆቻችን ማስረከብ እንችላለን ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ከወዳጆቿ ጋር ለመስራት ሁሉም በሯ ክፍት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለጠላቶቻችን መንግስት የኢትዮጵያን ጥቅም፣አንድነት እና ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ አንተኛም ብለዋል። የኢትዮጵያ ብልጽግና እና እድገት የማረጋገጥ ጉዞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና ይህንን የሚያቆም የትኛውም ኃይል እንደሌለ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ትናንት ላይ ቆማ የቀረች ሀገር አይደለችም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ነገን የዋጀ አቅም መገንባቷን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሰላም፣አንድነት እና ብልጽግና በኢትዮጵያውያን የጋራ ትብብር እውን ይሆናል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለሁሉ የምትበቃ እና ለሁሉም የምትሆን ለማድረግ በትጋት እንደሚሰራ አመልክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በክልሉ የዳበሩ የግጭት መፍቻ ስርዓቶችን በአግባቡ መጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው-ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ
Jan 24, 2026 78
አዲስ አበባ፤ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የዳበሩ የግጭት መፍቻና የፍትሕ ስርዓቶችን በአግባቡ መጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ ገለጹ። በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትብብር “የሕግ የበላይነትና አማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴዎች - ለዘላቂ ሰላም እና ዕድገት” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ከትናንት በጎ ዕሴቶችን መውሰድ፤ዛሬ ጠቃሚ አዳዲስ ዕሴቶችን መገንባት፤ ነገ ኢትዮጵያ እንድትበለጽግ የሚያደርጓት ቁልፍ ተግባራት ናቸው-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በክልሉ የፍትሕ ተቋማትን ተምሳሌትና የልምድ ተሞክሮ መቅሰሚያ የሚያደርጉ ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎች እየተከናወኑ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በመድረኩ ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ እንደገለጹት፤ በክልሉ ያሉ የዳበሩ የግጭት መፍቻና የፍትሕ ሥርዓቶችን በአግባቡ መጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው ብለዋል። በኮንፍረንሱ የተነሱት የህግ የበላይነት፣ አማራጭ የልዩነት መፍቻ መንገዶች፣ የዘላቂ ሰላምና የዘላቂ ልማት አጀንዳዎች አንገብጋቢና ወቅታዊ ናቸው ብለዋል። በሀገራችን ከለውጡ ወዲህ ከአጀንዳዎች ሁሉ ከፍ ብሎ የመጣው የመልማትና ሁለንተናዊ የብልፅግና አጀንዳ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ኢትዮጵያን በታሪክ ከምትጠቀስባቸው የግጭትና የድህነት አዙሪት አላቅቆ የበለፀገችና ለሌሎች ምሳሌ የሆነች ሀገር ለመገንባት ከፍተኛ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ከፍተኛ የልማት አጀንዳ በተቀሰቀሰበት በዚህ ወቅት በንግግር ሊፈቱ የሚችሉ ጉዳዮችን በኃይል ለማስፈጸም የሚሞክሩ አካላት የህብረተሰቡን ሰላም የሚነሱና የመልማት ፍላጎት የሚገቱ ችግሮችን መፍጠራቸውን ተናግረዋል። ልማት ሰላም ይፈልጋል ያሉት ሚኒስትሩ፥ የለውጡ መንግሥት ስለ ሰላም የዕይታና የፖሊሲ ለውጥ በማድረግ ዘላቂ ሰላምን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት አካሄድን ቀዳሚ አማራጭ ማድረጉን ጠቅሰዋል። የማንግባባባቸው ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሀገራዊ ምክክርና የሽግግር ፍትሕ መዘርጋቱን አንስተው፥ መንግሥት ሁልጊዜም ችግሮች በሰላማዊ መንገድ በውይይት እንዲፈቱ ባለው ፅኑ አቋም ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪዎችን ማድረጉን አስረድተዋል። በአማራ ክልል የሰላም አማራጭን መርጠው ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ የተመለሱ አካላት ለዘላቂ ሰላም ግንባታው ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና የልማት ሥራዎች መሳካት ትልቅ ሚና እንደሚኖረው አብራርተዋል። በመሆኑም የታሪክና የትውልድ ተጠያቂነትን ከሚያስከትል ጥፋት በመቆጠብ መንግሥት ለሰላም የሰጠውን ዕድል በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም በጎ ሚና መጫወት እንደሚገባም ተናግረዋል። ከሰባ በላይ አማራጭ ባህላዊ የግጭትና የችግር መፍቻ ስርዓቶች መኖራቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፥ በአማራ ክልልም ለባህላዊ ስርዓቶች የተሰጠው ትኩረት የሚበረታታ ነው ብለዋል። የዳበሩ የግጭት መፍቻና የፍትሔ ስርዓቶችን በአግባቡ መጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑንም ጠቅሰዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ከትናንት በጎ ዕሴቶችን መውሰድ፤ዛሬ ጠቃሚ አዳዲስ ዕሴቶችን መገንባት፤ ነገ ኢትዮጵያ እንድትበለጽግ የሚያደርጓት ቁልፍ ተግባራት ናቸው-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jan 24, 2026 93
አዲስ አበባ፤ጥር 16/2018(ኢዜአ)፦ከትናንት በጎ ዕሴቶችን መውሰድ፤ዛሬ ጠቃሚ አዳዲስ ዕሴቶችን መገንባት፤ ነገ ኢትዮጵያ እንድትበለጽግ የሚያደርጓት ቁልፍ ተግባራት ናቸው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዛሬ በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋራ ትብብር "የሕግ የበላይነትና አማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች - ለዘላቂ ሰላም እና ዕድገት" በሚል የተዘጋጀውን ዓለም አቀፍ ጉባኤን አስጀምረዋል።   በዚህ ወቅት፥ ኢትዮጵያ መደበኛ የፍርድ ተቋማቷን ብታዘምንም አብዛኛው ሕዝባችን ችግሩን የሚፈታበት ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓት ግን ተገቢው ቦታ ሳይሰጠው ቆይቷል ብለዋል፡፡ የባሕርዳር በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን አሟልቶ እየተጠናቀቀ ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አሁን ግን በሀገራችንም ሆነ በክልላችን ተደራሽ፣ ቅቡልነት ያለው እና በመርሕ ላይ የቆመ ፍትሕን ለማስፈን እንዲቻል መደበኛና ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶች ተጣጥመውና ተናብበው የሚጓዙበትን ዐውድ መፍጠር የግድ የሚልበት ወቅት ላይ እንገኛለን ነው ያሉት፡፡ ለዚህ ደግሞ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓቶቻችንን ከዘመናዊ ዕሳቤዎች ጋር ማስተሣሠር፣ በሕግ መደገፍ እና አሠራሮቻቸውን ማዘመን፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከምንተገብራቸው ሪፎርሞች ጋር አሠናስሎ ማዋወቀር ለነገ የማይባል ሥራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የጎደላቸውን ሞልተን በትክክል ከተጠቀምንባቸው፣ በጉዳዮች ብዛት በከፍተኛ ጫና ውስጥ የሚገኙ መደበኛ የፍትሕ ተቋሞቻችንን ትርጉም ባለው ደረጃ ያግዛሉ፤ በማኅበረሰቡ ዘንድ የተሻለ ተቀባይነት እና የባለቤትነት ስሜት የሚንጸባረቅባቸውን መፍትሔዎች ያቀርባሉ። ይህ ኮንፈረንስ ይሄንን አዎንታዊ ጥምረት ለመፍጠር የተሻለውን መንገድ እንደሚጠቁም እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ማህበራዊ
በክልሉ የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭን ለመቅረፍ ምግብና ስርዓተ ምግብ ላይ ይሰራል
Jan 25, 2026 42
አዳማ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭ ችግሮችን ለመቅረፍ ለምግብና ስርዓተ ምግብ ትኩረት መሰጠቱን በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ ገለፁ። የኦሮሚያ ክልል የምግብና ስነ ምግብ ምክር ቤት በክልሉ የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭን ችግሮችን ለመቅረፍ እየተከናወኑ ባሉ ስራዎች ላይ የምምክር መድረክ በአዳማ አካሄዷል ። በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ እንደገለፁት በክልሉ የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭ ችግሮችን ለመቅረፍ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ።   በተለይም ችግሩን ለመቅረፍ ለምግብና ስርዓተ ምግብ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰዋል። የኦሮሚያ የምግብና ስነ ምግብ ምክር ቤትም እስከ ወረዳ ድረስ አደረጃጀት በማዋቀር በቀዳማይ ልጅነት ልማት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም ከጽንስ እስከ ስድስት ዓመት ዕድሜ ያሉ ሕጻናት በአዕምሮ እና በአካል እንዲበለጽጉ የማድረግ ዓላማን አንግቦ ተግባራዊ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ በዚህም በምግብና ስነ ምግብ እጥረት የሚከሰቱ የመቀንጨርና የመቀጨጭ ችግሮችን ለመቀነስ በእናቶች፣ በቤተሰብ ምጣኔ፣ በግብርና፣ በትምህርትና በኢኮኖሚያዊ መስኮች ላይ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። መድረኩም በክልሉ የምግብና ስርዓተ ምግብ ችግሮችን ለመቅረፍ የተሰሩ ስራዎችን በአግባቡ በመፈተሽ በቀጣይ የተቀናጀ ጥረት ለማድረግ መሆኑንም አስገንዝበዋል ።   በሰቆጣ ቃልኪዳን የሞዴል ወረዳዎች ኢንሼቲቪ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ እስራኤል ሃይሉ በመድረኩ ላይ ባቀረቡት ጽሁፍ እንዳመለከቱት የሰቆጣ ቃልኪዳን በሁሉም ክልሎች ከ500 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች የህፃናት መቀንጨርና መቀጨጭ ችግሮችን ለመቅረፍ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የህፃናትን መቀንጨር ዜሮ ለማድረግ በተጀመሩ ስራዎች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ጠቁመዋል ። ለዚህም በመደኛነት እየተከናወኑ ካሉት ስራዎች መካከል በምግብና ስርዓተ ምግብ ውጤታማ ለማድረግ በወተት፣ በማር፣ በዶሮ፣ ዓሣ ልማት ላይ መሰራቱን አንስተዋል።    
በክልሉ የጤና ተቋማትን አገልግሎት አስጣጥ ለማሳደግ ለህብረተሰብ ተሳትፎ ትኩረት ተሰጥቷል
Jan 25, 2026 36
አዳማ ፤ጥር 17/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል የጤና ተቋማትን አገልግሎት አስጣጥ ለማሳደግ ለህብረተሰብ ተሳትፎ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ቡድን በምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሰትና ሉሜ ወረዳዎች በመገኘት በጤና አገልግሎት በተሰሩ ሞዴል ስራዎች ላይ የልምድ ልውውጥ አድርጓል። የኦሮሚያ ጤና ቢሮ አማካሪ አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ለኢዜአ እንዳሳታወቁት በክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራት፣ ፍትሃዊነትና ደህንነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው። ለስኬቱም የጤና ተቋማትን በግብአትና በሰው ሀይል ለማሟላትና ጽዱ ለማድረግ ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።   የጤና ተቋማቱን አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመንና የመድሀኒት አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ የማህበረሰብ መድሀኒት ቤቶች በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ መገንባታቸውን አመልክተዋል። የማህበረሰቡን የጤና ዋስትና ለማረጋገጥም በአነስተኛ ክፍያ ዓመቱን ሙሉ የህክምና አገልግሎት ማግኘት እንዲችል የጤና መድህን አገልግሎት ማስፋፋት መቻሉንም ጠቅሰዋል። በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች አማካኝነትም ቤት ለቤት ትምህርት በመስጠት ህብረተሰቡ ከተላላፊና ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች እራሱን እንዲከላከል እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የምስራቅ ሸዋ ዞን ጤና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን አብሬ በበኩላቸው በዞኑ ጠንካራ የጤና አገልግሎትን ለመገንባት ከህበረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በተሰራው ስራም የዞኑ ሆስፒታሎች፣ ጤና ጣቢያዎችና ጤና ኬላዎች ሞዴል ሆነው እንዲወጡ መሰራቱን ተናግረዋል። በሆስፒታል ደረጃ ሲሰጡ የነበሩ አልትራሳውንድ የመሳሰሉ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችን በ46 ጤና ጣቢያዎች በሟሟላት ህብረተሰቡን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ጠቅሰዋል። የጤና አገልግሎት መረጃን ዲጂታላይዝድ ማድረግና ተቋማቱን በማስዋብ ለተገልጋይና ለባለሙያዎች ምቹ ማድረግ ላይ መሰራቱን ገልፀዋል ። በምስራቅ ሸዋ ዞን የቦሰት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጉተማ ቢፍቱ የዲጂታል ጤና ቴክኖሎጂ ሥርዓትን ከማጠናከር እንዲሁም ህክምና አገልግሎትን ከማዘምን ረገድ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በተለይ በህክምና ተቋማት የሚስተዋሉ የህክምና ግብዓቶችን ከሟሟላት ባለፈ ጤና ተቋማትን ለማስዋብ ከወረዳው በጀት መመደቡን ጠቅሰው ጤና ተቋማትም የውሰጥ ገቢያቸውን እንዲጠቀሙ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል። የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጤና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ፉአድ ጁአድ በሰጡት አስተያየት በቦሰት ወረዳ እና ወለንጪቲ ከተማ የሚገኙ ሞዴል ጤና ጣቢያና ጤና ኬላ አገልግሎት አሰጣጡ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል ። በህክምና ተቋማቱ በተደረገው ሪፎርም የጤና ተቋማት በዘመናዊ መሳሪያዎችና በሰው ሃይል በሚገባ መደራጀታቸውን፣ ለተገልጋይና ለባለሙያዎች ምቹና ማራኪ መደረጉን መመልከታቸውን ጠቅሰዋል። በልምድ ልውውጡ ያገኙትን ተሞክሮ ወደ ዞኑ ጤና ተቋማት ወስደው በተግባር ለማዋል እንደሚሰሩ አመላክተዋል።        
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ  ብቃት ያለው የሰው ሃይል የማፍራትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል
Jan 25, 2026 61
አዲስ አበባ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ብቃት ያለው የሰው ሃይል የማፍራትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ዛሬ የክልሉ መንግስት በ60 ሚሊየን ብር ወጪ ያስገነባው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በፕሮፌሰር ገቢሳ እጄታ እናት ስም ተመርቆ ለማህበረሰቡ አገልግሎት ክፍት ሆኗል።   የቢሮ ኃላፊው ቶላ በሪሶ(ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ብቃት ያለው የሰው ሃይል የማፍራትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል። በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ቡኡራ ቦሩ በተሰኙ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ለመማር ማስተማር ስራው መሰረታዊው ጉዳይ የትምህርት ቤቶች ደረጃን የማሻሻሉ ተግባርም መሆኑንም ገልጸዋል።   ትውልዱ በእውቀት ተመራምሮ ለሀገሩና ለዓለም ውጤት ለማስገኘት ጠንክሮ መማር እንዳለበት የገለጹት ደግሞ ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጄታ ናቸው። የተገነባው ትምህርት ቤት ለዚሁ አጋዥ መሆኑና በእናታቸው ስም መሰየሙ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል። በቀጣይም ትምህርት ቤቱን ይበልጥ በቴክኖሎጂ በማደራጀት የምርምርና የልህቀት ማዕከል ሆኖ እንዲቀጥል ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር እንደሚሰሩም ፕሮፌሰሩ ጠቁመዋል።   የምዕራብ ሸዋ ዞን ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ባንዲራ ጋላና፣ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን የመገንባትና ያሉትን የማስፋፋት ስራዎች በሰፊው እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የትምህርት ቤቱ መገንባት በአካባቢው የነበረውን የትምህርት ቤቶች እጥረት በመቅረፍ ጥራት ያለው ትምህርት ለመስጠት ያስችላል ሲሉም አስረድተዋል። ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤትም የተማሪዎች መማሪያ ክፍል፣ የአስተዳደር ሕንፃና ሌሎች አገልግሎት መስጫዎችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።   በምረቃው ላይ የተገኙት የአካባቢው ነዋሪዎችም ኦሎንኮሚ ሞቱ አያኖ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአካባቢያቸው ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ልጆቻቸው ጥራት ያለው ትምህርት በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል። ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ትምህርት ቤት በክልሉ ምዕራብ ሸዋ ዞን ኤጄርሳ ላፎ ወረዳ ሲሆን መታሰቢያነቱም ለእናታቸው ወይዘሮ ሞቱ አያኖ መሆኑ ታውቋል።
የአዲስ አበባ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስኬቶች የኢትዮጵያን የውበት ልክና መልክ የሚያስተዋውቁ ናቸው - የመዲናዋ ነዋሪዎች
Jan 25, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስኬቶች የኢትዮጵያን የውበት ልክና መልክ የሚያስተዋውቁ መሆናቸውን የመዲናዋ ነዋሪዎች ገለጹ። አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብና ጽዱ ለማድረግ የተገነቡ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ የልማት ሥራዎች መዲናዋን በአጭር ጊዜ ውስጥ አስደናቂ ገጽታ አላብሰዋታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት በገበታ ለሸገር፣ በሰው ተኮር፣ በኮሪደር እና በወንዝ ዳርቻ ልማት የተገነቡ መሠረተ ልማቶች አዲስ አበባን የለውጥ ምሳሌ አድርገዋታል።   ይህም ለመዲናዋ ነዋሪዎች ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ምቹ ገጽታ በማጎናጸፍ ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ማዕከል ተወዳዳሪነትን የገለጡ ሆነዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎችም፤ የአዲስ አበባ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስኬቶች ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ታሳቢ በማድረግ ምቹ የከተሜነት ምኅዳር የፈጠሩ ናቸው ብለዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ኢንጂነር ሳምሶን ወልደማሪያም እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ወንዞች ያጋጥማቸው የነበረው ብክለት ለነዋሪዎች የጤና መታወክ መንስኤ እንደነበር አስታውሰዋል። በዚህ መነሻነትም በኮሪደር እና በወንዝ ዳርቻ ልማት የተገኙ የልማት ውጤቶች በመዲናዋ የነዋሪዎችን እንቅስቃሴ የሚያሳልጥ ምቹ የከተሜነት ምኅዳር እንዲፈጠር ማድረጉን ገልጸዋል። በመዲናዋ በሁሉም አካባቢዎች ጽዱና ምቹ የመዝናኛ ስፍራ መፈጠራቸው ነዋሪዎች የአዕምሮ እረፍት የሚያገኙበትን ዕድል እንደፈጠረ ተናግረዋል። የወንዝ ዳርቻ እና መዲናዋን የማስዋብ የልማት ስኬቶች የኢትዮጵያን ገናና የስልጣኔ ታሪክና ማንነት በልኩ በመግለጥ በሀገር ገጽታ ግንባታ ላይ ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው አንስተዋል።   ሌላኛው አስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪ ዘሪሁን ተስፋዬ በበኩላቸው፤ በአዲስ አበባ መንፈስን የሚያድስ የጥሞና ጊዜ ማሳለፊያ ምቹ የመዝናኛ ስፍራዎች ተፈጥረዋል ብለዋል። የመዲናዋ ውብ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች የጥበብ ስራዎቻቸውን መስራት የሚሹ ሙያተኞች በአቅራቢያቸው የሚሰሩበትን ጥሩ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸውም ገልጸዋል።   ከተማዋ ሀገር ተረካቢ ለሆኑ ህፃናትም ምቹ የመዝናኛ ስፍራዎችን አዘጋጅታለች ያሉት ደግሞ ካዛንቺስ አካባቢ አካባቢ በሚገኘው የመዝናኛ ስፍራ ልጆቹን ሲያጫውቱ ያገኘናቸው ናትናኤል መላኩ ናቸው። ህጻናትን ታሳቢ ያደረጉ የመዝናኛ ስፍራዎች ልማት መኖራቸው ልጆች ጤናቸው በሚጠበቅበትና ለአደጋ አጋላጭ ባልሆኑ ቦታዎች ጥሩ ጊዜ ከቤተሰብ ጋር እንዲያሳልፉ ያደርጋል ነው ያሉት።   አቶ አብነት ሹምባሽ በበኩላቸው ይህ አስደናቂ ልማት የዜጎችን ጤና ከማስጠበቅ ባለፈ እንደ አፍሪካ መዲናነት የኢትዮጵያን መልክና ውበት በሚገባ የሚያስተዋውቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
የሌማት ትሩፋትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ለማር ምርታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው
Jan 25, 2026 61
አዲስ አበባ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦የሌማት ትሩፋትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ለማር ምርታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር ገለፀ። የኢትዮጵያ ምቹ የአየር ጠባይና የአረንጓዴ አሻራ የደን ሽፋን ዕድገት የበርካታ ዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል። በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ አማካሪ ግርማ ሙሉጌታ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የግብርና ምርታማነትን ማሻሻል መርሃ ግብሮች በማር ምርታማነት ላይ እመርታዊ ውጤት እያስገኘ ነው። በተለይም የሌማት ትሩፋትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች የዜጎችን የንብ ማነብ ተነሳሽነት በማሳደግ በማር ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ውጤት አንዲመዘገብ እያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ የማር ምርታማነትም ዜጎች የተመጣጠነ የምግብ ሥርዓት የሚያገኙበትን አማራጭ በመፍጠር የውጭ ምንዛሬ ገቢ ጭምር እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም የዜጎችን የንብ ማነብ የሥራ ባህል በማሳደግ የማር ምርታማነትን ማሻሻል የሚያስችል ምኅዳር የመፍጠር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አንስተዋል። በማር ምርታማነት ለተመዘገበው ስኬትም የንብ አናቢዎች ዘመናዊ የአመራርት ዘዴ የግንዛቤ ማስጨበጫና የግብዓት አቅርቦት መሻሻል ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚህም ባለፈው በጀት ዓመት 326ሺህ ሜትሪክ ቶን የማር ምርት በመሰብሰብ በተያዘው በጀት ዓመት 375 ሺህ ሜትሪክ ቶን የማር ምርት ለመሰብሰብ በተያዘው ዕቅድ መሠረት አበረታች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። የማር ምርት በጥራትና በብዛት በማምረት የውጭ ገበያ የማር ምርት አቅምን ለማሳደግ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።   የኢትዮጵያ ንብ ሃብት ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ነጋሽ በቃና በበኩላቸው፤ መንግስት ለግብርና ምርታማነት የሰጠው ትኩረት በማር ምርታማነት ላይ ውጤት እንዲገኝ እያስቻለ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራና የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሮችም በርካታ ዜጎች በንብ ማነብ የሥራ መስክ በመሰማራት የማር ምርታማነት ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የድርሻውን እንዲወጣ እያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።    
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የራስን ተፈጥሯዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ-ምድራዊና ታሪካዊ ሃብት ምላሽ የማስገኘት ምክንያታዊ የሕልውና ጉዳይ ነው
Jan 25, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የራስን ተፈጥሯዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ-ምድራዊና ታሪካዊ ሃብት ምላሽ የማስገኘት ምክንያታዊ የሕልውና ጉዳይ መሆኑን ምሁራነ ገለጹ። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቂያና የጋራ ትርክት መገንቢያ መሆኑንም የተናገሩት። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ-ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ የህልውና ጥያቄ መሆኑ ይታወቃል። በኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራንም፤ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን እንድታጣ የተደረገችበት ታሪካዊ ሴራ የሚያስቆጭ መሆኑንም ገልጸዋል።   የባህልና ታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አህመድ ዘካርያ፤ የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ማንነትና ስልጣኔ ከቀይ ባሕር ባለቤትነት ጋር በእጅጉ ጥብቅ ቁርኝት አለው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም የራስን ተፈጥሯዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ-ምድራዊና ታሪካዊ ሃብት ምላሽ የማስገኘት ምክንያታዊ የሕልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ምላሽ የማስገኘት ቀጣናዊና አሕጉራዊ ሰላምና ደኅንነትን በማስጠበቅ ለፍትሐዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ዕድገት መሠረት እንደሚሆን ተናግረዋል። ኢትዮጵያውያንም የሀገራቸውን ሉዓላዊነት፣ ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስከብሩ ጽኑ ህዝቦች መሆናቸውን የዓድዋ ድል ሕያው ምስክር መሆኑን አስታውሰዋል። የጋራ ተግባቦት ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ዓይነተኛ ሚና አለው ያሉት ምሁሩ፤ አሰባሳቢ ትርክት ግንባታም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። በዚህም የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ለማስገኘት በሚደረገው ጥረት ሁሉም ዜጋ በከፍተኛ የኃላፊነት መንፈስ በመተባበር ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር መስራት እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። በአሁኑ ወቅትም የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ምላሽ ለማስገኘት የሚደረገው ጥረት የሀገርን ዕድገትና ቀጣዩን ትውልድ ታሳቢ ያደረገ ወሳኝ ብሔራዊ አጀንዳ መሆኑንም አስረድተዋል።   በውጪ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ተመራማሪ ጋሻው አይፈራም(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ታሪክና ስልጣኔ ከባሕር በር ባለቤትነት ጋር የተሰናሰለ ነው ብለዋል። ለአብነትም ከአክሱም ዘመነ መንግሥታት ጀምሮ ለበርካታ ሺህ ዘመናት ያህል ቀይ ባሕር የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ወሰንና የግዛት መዳረሻ አካል ሆኖ እንደቆየ አስታውሰዋል። በታሪካዊ ጠላቶች ሴራ እና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በቅጡ ባልተገነዘቡ ውስን ቡድኖች አማካኝነት ኢትዮጵያ ከተፈጥሯዊ የባሕር በር ወሰኗ እንድትገለል መደረጉን አስታውሰዋል። በዚህም የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሕጋዊ፣ ሥነ-ልቦናዊ፣ መልክዓ-ምድራዊ እና ፍትሕዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ትክክለኛና ምክንያታዊ ጥያቄ መሆኑን ተናግረዋል።
በድሬዳዋ በበጀት አመቱ ስድስት ወራት ከ48 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ስራ ገብተዋል
Jan 25, 2026 45
ድሬዳዋ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ አስተዳደር በተያዘው በጀት ዓመት ያለፉት ስድስት ወራት ከ48 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ስራ መግባታቸውን የንግድ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ። በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የኮሪደር ልማትና መሠረተ ልማት ስራዎች የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እንዲጨምር ከፍተኛ ሚና እያበረከቱ ናቸው።   በቢሮው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ጥናት መረጃ ዝግጅት ቡድን መሪ አበራ መንግሥቱ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በበጀት አመቱ ስድስት ወራት ከ48 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 251 የሀገር ውስጥ እና የውጭ ባለሃብቶች ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ገብተዋል። ፈቃድ ከወሰዱ አልሚዎች መካከል በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 10 የሚሆኑት ኢንዱስትሪዎች ማምረት መጀመራቸውንና ለ1ሺህ 800 ዜጎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል። በግማሽ በጀት ዓመቱ ወደ ስራ የገቡ አልሚዎችም በማኑፋክቸሪንግ፣ በአገልግሎት፣ በኮንስትራክሽንና በግብርና ዘርፎች መሰማራታቸውን ገልጸው በዚህም ከ13 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዚያዊ የስራ ዕድል ይፈጥራሉ ብለዋል። እንደ አቶ አበራ ገለፃ ድሬዳዋ ለጅቡቲ ወደብ ያላት ቅርበት፣ አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ እንዲሁም በፌዴራል እና በአስተዳደሩ ለባለሃብቶች የሚደረገው ድጋፍ ለኢንቨስትመንት ፍሰቱ መጨመር አስተዋጽኦ እያበረከቱ ናቸው። እንዲሁም ባለፉት የለውጥ አመታት የተዘረጉ መሠረተ ልማቶች፣ የኮሪደር ልማት እና ነፃ የንግድ ቀጣናው ለኢንቨስትመንት ስራ የሚመጡ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በከፍተኛ ደረጃ እንዲጨምሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን ገልጸዋል።   በድሬዳዋ ኢንቨስት ለሚያደርጉ ባለሃብቶች ልዩ ድጋፍ መደረጉን የተናገሩት ደግሞ የአስተዳደሩ የመሬት ልማትና ማኔጀመንት ቢሮ ኃላፊ ሳጅድ አልይ ናቸው። ባለሃብቶች የሚሰጣቸውን መሬት ለታለመለት አላማ በፍጥነት እንዲያውሉ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝም ጨምረው ተናግረዋል። የኤ ኤም ሞተርስ የመኪና መገጣጠሚያ ኢንዱስትሪ ስራ-አስኪያጅ አለማየሁ ሚደቅሳ፤ በተሰጣቸው ምቹ ቦታ የከባድ መኪና እና ለህዝብ ትራንስፖርት የሚውሉ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን ለመገጣጠም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
በሐረሪ ክልል የተዘረጉ ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥና የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት እያጎለበቱ መጥተዋል
Jan 25, 2026 136
ሐረር ፤ጥር 17/2018(ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል የተዘረጉ ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥና የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት እያጎለበቱ መምጣታቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። የህዝቡን የልማትና የአገልግሎት አሰጣጥ ተግባራት በቅንጅት በማከናወን የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ተናግረዋል። የሐረሪ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስ እና ሰው ሃብት ቢሮ በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ህዝባዊ መድረክ አካሂዷል።   የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በክልሉ የተከናወኑ የልማትና የአገልግሎት አሰጣጥ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። ከተሳታፊዎቹ መካከል አቶ ኡስማን ዩስፍ እንዳሉት በክልሉ ህዝቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የነዋሪውን ተጠቃሚነት እያጎለበቱ መሆናቸውን ተናግረዋል። በከተማዋ የተከናወኑ እንደ ኮሪደር ልማት ስራዎች እና ሌሎች ልማቶች የህዝቡን ጥያቄ የመለሱ በመሆኑ እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል። የነዋሪው ጥያቄ የነበሩ የመንገድና የኤሌክትሪክ አገልግሎት መፍትሄ አግኝተዋል ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ፋንቱ እሸቱ ናቸው።   ከተማዋን ውብ እና ለጎብኚውም ሆነ ለነዋሪዎች ምቹ በማድረግ የቱሪስት ፍሰቱ እንዲጨምር በማድረጉ ለስራ እድል ፈጠራና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እየተሳለጡ መሆናቸውን ያወሱት ደግሞ ሻምበል ጋሻው ሙሉዓለም ናቸው። ይህም ተግባር የክልሉ አመራርና የህዝብ ቅንጅት ውጤት በመሆኑ በቀጣይም በትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና የዋጋ ንረትን የሚያባብሱ ነጋዴዎችን መቆጣጠር ላይ መጠናከር እንዳለበት ጠይቀዋል።   በክልሉ በማህበረሰብ ጤና መድህን እየተከናወነ የሚገኘው ስራ አቅመ ደካሞችን እያገዘ መሆኑንና በፍትህ አገልግሎት አሰጣጥም ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን በመቅረፋቸው ሊበረታቱ ይገባል ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ሳራ ይስሃቅ ናቸው።   በቀጣይም ያልተገባ ዋጋ በሸቀጦች ላይ በመጨመር ህዝቡን ለምሬት እየዳረጉ የሚገኙትን ስግብግብ ነጋዴዎችን የሚወሰደው ቁጥጥር እንዲጠናክር አመልክተዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በበኩላቸው ህዝቡ ከአገልግሎት አሰጣጥ፣ከልማት ተደራሽነትና ከኑሮ ውድነት ጋር ያነሳው ሃሳብን በዕቅድ በመያዝ ምላሽ እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል። የማህበረሰቡን ፍላጎት መሠረት ያደረገ የልማት ስራዎችም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። የዋጋ ግሽበትን ለመቅረፍ ምርታማነትን ማሳደግና ስግብግብ ነጋዴዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።      
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢኒስቲትዩቱ ይፋ ያደረገው የእንሰት መፋቂያ ቴክኖሎጂ የሥራ ጫናን ከማቅለል ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጥሯል
Jan 24, 2026 74
ሀዋሳ፤ጥር 16/2018 (ኢዜአ)፦የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ጋር በመቀናጀት ይፋ ያደረገው የእንሰት መፋቂያ ቴክኖሎጂ የሥራ ጫናን ከማቃለል ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። የቋሚ ኮሚቴው አባላት በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ በኢንስቲትዩቱ የተሰራ ዘመናዊ የእንሰት መፋቂያ ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራን ተመልክተዋል። የቋሚ ኮሚቴው ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺ ሀሰን በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፣ኢንስቲትዩቱ የህብረተሰቡን ኑሮ የሚያቃልሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እያፈለቀ ይገኛል።   ከእነዚህ ውስጥ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን የስራ ጫና የሚያቃልል የእንሰት መፋቂያ፣ መጭመቂያና መቁረጫ መሳሪያ አንዱ ነው ብለዋል። በርካታ ሴቶች በእንሰት ሥራ እንደሚሰማሩ ገልጸው፣ እንዲህ አይነት ቴክኖሎጂዎች መምጣታቸው የሥራ ጫናውን ከማቃለል ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ፈጣን እድገት ለአፍሪካ ሀገራት አብነት ይሆናል - የአፍሪካ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች
Jan 23, 2026 143
አዲስ አበባ፤ ጥር 15/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር ኃይል ፈጣን እድገት ለአፍሪካ ሀገራት አብነት ይሆናል ሲሉ የአፍሪካ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት ክብረ በዓልን በማስመልከት የተዘጋጀው የአቪዬሽን ኤክስፖ ተከፍቷል።   ኤክስፖው የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ኤክስፖውን የጎበኙ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች፤ የኢትዮጵያ አየር ሃይል ለአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ በሚሆን አግባብ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ስለመሆኑ መታዘባቸውን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የቦትስዋና ኤምባሲ ወታደራዊ አታሼ ኮሎኔል ሞታሲ ቼሌኒያኔ፤ የኢትዮጵያ አየር ሃይል በአቪዬሽን፣ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ዘርፍ አስደማሚ ለውጥ ውስጥ መሆኑን ከኤክስፖው መመልከታቸውን ገልጸዋል።   በተለይ አየር ኃይሉን ጥገናን ጨምሮ በሌሎች ቁልፍ የዘርፉ ምህንድስና ስራዎች ራሱን ለመቻል እያከናወነ ያለው ስራ የሚደነቅ መሆኑን አንስተው፤ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከዚህ ልምድ መውሰድ እንዳለባቸው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የናሚቢያ ኤምባሲ ወታደራዊ አታሼ ማካንዚ ቺቤራ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ባለፉት ጊዜያትም ሆነ አሁን ላይ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የራሱን እና የአፍሪካን አቅም ለማሳደግ ጥረት እያደረገ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት በጋራ እና በትብብር ከሰሩ ብዙ ርቀት መሄድ እንደሚችሉ ጠቁመው፤ በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ አየር ሃይል የወሰደውን ተነሳሽነት አድንቀዋል።   በኢትዮጵያ የጋቦን ኤምባሲ ወታደራዊ አታሼ ኮሎኔል አርሲዴ አንጉሌ፤ የኢትዮጵያ አየር ሃይል ሀገር የሚወክል ተቋም እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል። ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ጥሩ ምሳሌ ነው ብለዋል።
የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ሥራችንን ለማዘመንና ለማቀላጠፍ አግዞናል -ሰልጣኞች
Jan 23, 2026 167
ወልቂጤ፤ ጥር 15/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮ-ኮደርስ ያገኙት ስልጠና የዲጂታል ክህሎታቸውን በማሳደግ ሥራቸውን ለማዘመንና ለማቀላጠፍ እንዳገዛቸው በወልቂጤ ከተማ የኮደርስ ሰልጣኞች ገለጹ። መንግስት ለዜጎች ያመቻቸው የአምስት ሚሊዮን የኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና ዜጎች ከዲጂታል ዓለሙ ጋር ለመራመድ የሚያስችላቸውን የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት እያስጨበጣቸው ነው። በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ተቋማት የሚሰሩ ሠራተኞችም ስልጠናውን እንዲወስዱ በአስተዳደሩ የተመቻቸላቸውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የዲጂታል እውቀታቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። ስልጠናውን የወሰዱት ሠራተኞች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በኢትዮ-ኮደርስ በተለያዩ ዘርፎች ያገኙት ስልጠና የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን በማሳደግ ሥራቸውን እንዲያዘምኑና ውጤታማ እንዲሆኑ እያገዛቸው ነው።   በወልቂጤ ከተማ የኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት ባለሙያ ወጣት ሰለሞን ደርብ በኢትዮ ኮደርስ በዳታ ፕሮግራሚንግ፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎትና በአንድሮይድ ዘርፎች ስልጠና ወስዶ ክህሎቱን ማሳደጉን ተናግሯል፡፡ በአሁኑ ወቅትም በሌሎች ዘርፎች ተጨማሪ ስልጠና እየወሰደ መሆኑን ጠቁሞ፣ በኮደርስ ስልጠና ባገኘው እውቀት በትርፍ ሰአቱ ተጨማሪ ሥራ ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ተናግሯል። የከተማው ሳይንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽህፈት ቤት ባለሙያ ወጣት ጅብሪል መጀል በበኩሉ፤ የዲጂታል እውቀቱን ለማሳደግ የሚያግዘውን የኮደርስ ስልጠና በመውሰድ ከራሱ ባለፈ ሌሎችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ተናግሯል።   ያገኘው ስልጠና በኮምፒውተር ሳይንስ በዲግሪ ለመማር መነሳሳት እንደፈጠረለት ገልጾ፣ በቀጣይም በተለያዩ ዘርፎች የሚሰጠውን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰዱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጿል። በማይክሮ ሶፍት መተግበሪያዎች በወሰደው ስልጠና ያገኘውን እውቀትና ክህሎት በተቋም ሥራ በመተግበር ሥራውን ለማቀላጠፍና ለችግር መፍቻነት እየተጠቀመበት መሆኑን ተናግሯል። በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ያለንን እውቀትና ክህሎት በማሳደግ ከዲጂታል ዓለም ፈጣን እድገት ጋር ለመጓዝ የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛዋ ሰልጣኝ ወይዘሮ አቻምየለሽ ዘርጋ ናቸው።   ስልጠናው ከኋላቀር የመረጃ አያያዝ ስርዓት በማላቀቅ የግልና የመስሪያ ቤት መረጃዎችን ለማዘመን የሚያስችል እውቀት እንዳገኙበት ተናግረዋል፡፡ በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በአራት የተለያዩ ዘርፎች የቀሰሙት እውቀት በቴክኖሎጂ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያ እንዳደረጋቸው የተናገሩት ደግሞ የከተማው ንግድና ገበያ ልማት ባለሙያ አቶ ጅላሉ ሙዘይን ናቸው ። ስልጠናው የተለያዩ አገልግሎት የሚሠጡ ሶፍትዌሮችን አበልጽገው እንዲጠቀሙ እድል መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡   የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሃምዱ ካሚል፤ በከተማው እስካሁን ድረስ 20ሺህ የሚጠጉ ዜጎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደው የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣይ ስልጠናውን በሁሉም የመንግስት መዋቅር ተደራሽ በማድረግ ዜጎች የቴክኖሎጂ ክህሎትና ዕውቀታቸውን ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ኮሌጆች ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ለማሳካት  የማይተካ ድርሻ አላቸው
Jan 23, 2026 86
ቦንጋ፤ ጥር 15/2018(ኢዜአ)፦ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ለማሳካት በሚደረገው ርብርብ ብቃት ያለው የሰው ሀይል በማፍራት የማይተካ ድርሻ እንዳላቸው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኢትዮ ኮደርስ ስልጠናና ፋይዳ መታወቂያን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።   በመድረኩ የተገኙት የቢሮ ምክትል ሀላፊና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ምትኩ አስፋው እንደገለጹት፤ ኮሌጆች ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ለማሳካት በሚደረገው ርብርብ ብቃት ያለው የሰው ሀይል በማፍራት የማይተካ ሚና አላቸው፡፡ ለዚህም ራሳቸውን በቴክኖሎጂ ግብአቶች በማደራጀት ለሰው ሀይል ልማት ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው አክለዋል። ለዲጂታል ኢትዮጵያ መሳካት ድርሻ ላላቸው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እና ለፋይዳ መታወቂያ ኢንሼቲቮች ትኩረት መስጠት ሌላው ተግባራቸው መሆን እንዳለበትም አስገንዝበዋል። በክልሉ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በዓመት ከ110 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እስካሁን ድረስ 28 ሺህ 90 ሰዎች እንደወሰዱና 8 ሺህ የሚጠጉትም ሰርተፊኬት ማግኘታቸውን ገልጸዋል። ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ ከማድረግ አንጻር በዓመቱ ለማሳካት ከታቀደው ውስጥ እስካሁን ድረስ 246 ሺህ 436 ዜጎችን የመታወቂያው ባለቤት ለማድረግ መቻሉንም ጠቁመዋል። ሥራውን ለማሳካትም የአሁኑ የንቅናቄ መድረክ ተደማሪ አቅም ይሆናል ብለዋል።   በመድረኩ የተገኙት የካፋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ ተፈሪ ታደሰ በበኩላቸው፤ በዞኑ በኮደርስ ስልጠና በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሥራዎች እንደተጀመሩና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ኢንሼቲቮቹን ለማሳካት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከሁለተኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጋር በቅንጅት እንዲሰሩ መደረጉንም ጠቁመዋል።
ስፖርት
በፕሪሚየር ሊጉ ባህር ዳር ከተማ ከሃዋሳ ከተማ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው 
Jan 25, 2026 54
አዲስ አበባ፤ ጥር 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል። ምሽት 12 ሰዓት ባህር ዳር ከተማ ከሃዋሳ ከተማ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ስታዲየም ይጫወታሉ። ባህር ዳር ከተማ በሊጉ እስከ አሁን 16 ጨዋታዎችን አድርጎ በአራቱ ሲያሸንፍ በሶስቱ ተሸንፏል። ዘጠኝ ጊዜ አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 11 ግቦችን ሲያስቆጥር 10 ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ21 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። ባህር ዳር ከተማ በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርካታ ጨዋታዎችን አቻ የወጣ ቡድን ነው። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ ካከናወናቸው 16 ጨዋታዎች መካከል ስምንቱን ሲያሸንፍ አራት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ አራት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። 18 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 10 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ሃዋሳ ከተማ በ28 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በጥሩ ወቅታዊ ብቃት ላይ የሚገኘው ሃዋሳ ከተማ ካሸነፈ ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ያደርጋል። ባህር ዳር ከተማ ከሁለት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። በሌላኛው መርሐ-ግብር አርባምንጭ ከተማ ከፋሲል ከነማ ከቀኑ 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አርባምንጭ ከተማ በሊጉ እስከ አሁን ምንም ጨዋታ ያላሸነፈ ብቸኛው ቡድን ነው። በስምንት ጨዋታዎች ሲሸነፍ በተመሳሳይ ስምንት ጊዜ አቻ ወጥቷል። አምስት ግቦችን ሲያገባ 17 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በስምንት ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። በውድድር ዓመቱ ካካሄዳቸው 15 ጨዋታዎች መካከል ስድስቱን ያሸነፈው ፋሲል ከነማ በበኩሉ አንድ ጊዜ ሽንፈት አጋጥሞታል። በስምንት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 10 ግቦችን በ15ቱ ጨዋታ ላይ ሲያስቆጥር አምስት ግቦችን አስተናግዷል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ፋሲል ከነማ በ26 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። አርባምንጭ ከተማ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን ለማግኘት ይጫወታል። ፋሲል ከነማ ማሸነፍ ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት እንዲመለስ ያደርገዋል። አዳማ ከተማ ከመቀሌ 70 እንደርታ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አዳማ ከተማ በ26 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። መቀሌ 70 እንደርታ በ16 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ጨዋታው ሁለቱም ቡድኖች በሊጉ ተከታታይ ድላቸውን ለማስመዝገብ የሚያደርጉት ነው። ከቀኑ 7 ሰዓት ሀዲያ ሆሳዕና ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ያለው ሀዲያ ሆሳዕና በ20 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ13 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሀዲያ ሆሳዕና ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ባለፉት ሰባት ጨዋታዎች ከድል የራቀው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ማሸነፍ ወደ ድል ይመልሰዋል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ሲዳማ ቡና ሊጉን በ33 ነጥብ እየመራ ነው። የቅዱስ ጊዮርጊሱ አቤል ያለው እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ አዲስ ግደይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በጋራ እየመሩ ነው።
የታሪካዊ ተቀናቃኞቹ አርሰናል እና ማንችስተር ዩናይትድ የዛሬ ምሽት ፍልሚያ
Jan 25, 2026 74
አዲስ አበባ፤ ጥር 17 /2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ23ኛ ሳምንት መርሃ ግብር አርሰናል እና ማንችስተር ዩናይትድ ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከምሽቱ 1 ሰዓት ከ30 በኤምሬትስ ስታዲየም ይደረጋል። አርሰናል በሊጉ ባደረጋቸው 22 ጨዋታዎች 15 ጊዜ ሲያሸንፍ 2 ጊዜ ተሸንፏል። 5 ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥቷል። መድፈኞቹ በጨዋታዎቹ 40 ጎሎችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፉ 14 ግቦችን አስተናግደዋል። በ43 ዓመቱ ስፔናዊ አሰልጣኝ ማይክል አርቴታ የሚመራው አርሰናል በ50 ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ተጋጣሚው ማንችስተር ዩናይትድ በውድድር ዓመቱ ባደረጋቸው 22 ጨዋታዎች 9 ጊዜ ሲያሸንፍ 5 ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪዎቹ 8 ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። ቀያዮቹ ሴይጣኖች 38 ጎሎችን ሲያስቆጥሩ 32 ግቦችን አስተናግደዋል። በ44 ዓመቱ እንግሊዛዊ ማይክል ካሪክ የሚሰለጥነው ማንችስተር ዩናይትድ በ35 ነጥብ 5ኛ ደረጃን ይዟል። ሁለቱ ክለቦች በሁሉም ውድድሮች ሲገናኙ የአሁኑ ለ246ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም በነበራቸው 245 የእርስ በእርስ ግንኙነቶች ማንችስተር ዩናይትድ 99 ጊዜ አሸንፏል። አርሰናል 91 ጊዜ ሲያሸንፍ 55 ጊዜ አቻ ወጥተዋል። በፕሪሚየር ሊጉ 66 ጊዜ ተጫውተዋል። ማንችስተር ዩናይትድ 25 ጊዜ ሲያሸንፍ አርሰናል በ23ቱ ድል ቀንቶታል። 18 ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች አርሰናል አራት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ነጥብ ተጋርተዋል። ዩናይትድ በሊጉ ለመጨረሻ ጊዜ አርሰናልን ያሸነፈው እ.አ.አ ሴፕቴምበር 4 2022 ሲሆን በወቅቱ የ 3 ለ 1 ድል ተቀዳጅቷል። አርሰናል እና ማንችስተር ዩናይትድ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ታሪካዊ ተቀናቃኞች የሚባሉ ቡድኖች ናቸው። ክለቦቹ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኙት እ.አ.አ በ1894 ነበር። በዚሁ ጨዋታ ቡድኖቹ ሶስት አቻ ተለያይተዋል። ቡድኖቹ ከመጀመሪያ ጨዋታቸው አንስቶ ለ131 ዓመታት የቆየ ፉክክር በእንግሊዝ እና በአውሮፓ መድረክ አድርገዋል። አርሰናል የሊጉን ዋንጫ 13 ጊዜ ሲያነሳ ማንችስተር ዩናይትድ 20 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። ጨዋታው አርሰናል ከሁለት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ፤ ዩናይትድ ከማንችስተር ደርቢ ድል በኋላ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ የሚያደርጉት ነው። የ41 ዓመቱ ክሬግ ፓውሰን የሁለቱን ክለቦች ተጠባቂ ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌሎች መርሃ ግብሮች ክሪስታል ፓላስ ከቼልሲ፣ ኒውካስትል ዩናይትድ ከአስቶንቪላ እና ብሬንትፎርድ ከኖቲንግሃም ፎረስት በተመሳሳይ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የተፋሰስ ልማት ሥራ የመሬት ለምነትን በመጨመር ምርታማነትን አሳድጓል
Jan 23, 2026 147
ሃዋሳ፤ ጥር 15/2018 (ኢዜአ):-የተፋሰስ ልማት ሥራ የአፈር መሸርሸርን በማስቀረትና የመሬት ለምነትን በመጨመር ምርታማነታቸውን በማሳደጉ ልማቱን አጠናክረው መቀጠላቸውን የሲዳማ ክልል አርሶ አደሮች ገለጹ፡፡ አርሶ አደሮቹ ለኢዜአ እንዳሉት ቀደም ሲል በተፋሰስ ልማት ያከናወኗቸው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎች የአፈር መሸርሸርን በማስቅረትና የመሬት ለምነትን በመጨመር ምርትና ምርታማነታቸውን እያሳደገው ነው። ተጠቃሚነታቸውን አጠናክሮ ለማስቀጠልም በአሁኑ ወቅትም የተፋሰስ ልማት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ከአርሶ አደሮቹ መካከል አቶ ቶማስ መራሳ እንደገለጹት በየዓመቱ በተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራ በመሳተፍ የአካባቢያቸውን ለምነት እየጠበቁ ነው፡፡ ተፋሰስ ልማቱ ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚ እያደረጋቸው በመምጣቱ በአሁኑ ወቅትም በቡድን ተደራጅተው ልማቱን እያከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ተከናውኖ ባገገሙ መሬቶችም ቡናና ፍራፍሬዎችን በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ሌላው አርሶ አደር ጴጥሮስ ሶቾሳ በበኩላቸው በተፋሰስ ልማት ሥራው አርሶ አደሩ በንቃት እየተሳተፈና ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ በአካባቢያቸው ከዚህ ቀደም ገላጣ የነበሩና የተጎዱ መሬቶች ማገገማቸውን ጠቅሰው፣ በእርሻ ማሳቸው የነበረውን ባህር ዛፍም በመንቀል የመሬታቸውን ለምነት እየጠበቁና ምርታማነት እያሳደጉ መምጣታቸውን ተናግረዋል። የተፋሰስ ልማት ሥራው ምርት የማይሰጡ መሬቶች ወደ ምርት እንዲገቡና የሥራ እድል እንዲፈጠር ማድረጉን የገለጹት ደግሞ ሌላው አርሶ አደር ሳሙኤል ጢሞቲዮስ ናቸው። ቀበሌያቸው ተዳፋታማ በመሆኑ ጎርፍ መሬታቸውን በመሸርሸር ለምነቱን እያጣ በመምጣቱ ከልማቱ ተጠቃሚ ሳይሆኑ መቆየታቸውን አስታውሰው፣ የተፋሰስ ልማት ሥራ ከተጀመረ ወዲህ በየዓመቱ ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።   የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ በየዓመቱ የተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች የተጎዳ መሬት እንዲያገግም ጉልህ አስተዋጾ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። የውሃ አማራጮችን በመጨመር የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጉልህ ሚና በመጫወታቸው ልማቱ በየዓመቱ እየተጠናከረ መምጣቱንም ገልጸዋል። በዚህም በክልሉ በየጊዜው በሚካሄዱ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ በክልሉ በዘንድሮ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራ ከ147 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የሚለማ ሲሆን በተለዩ 678 ንኡስ ተፋሰሶች ለ30 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ እንደሚከናወን ታውቋል።
ኢትዮጵያ በውኃ ሀብት አስተዳደር እና በተፋሰስ ልማት ሥራዎች ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ነው 
Jan 22, 2026 110
ነቀምቴ ፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በውኃ ሀብት አስተዳደርና በተፋሰስ ልማት ሥራዎች ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች መሆኑን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ በነቀምቴ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)፣ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት የውኃ ሀብትን በአግባቡ አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል የተወሰዱ እርምጃዎች ውጤት እያስገኙ ነው። ኢትዮጵያ የምትከተለው ፍትሃዊና ምክንያታዊ የውኃ ሀብት አጠቃቀምና አስተዳደርም የልማት እንቅስቃሴን ለማፋጠን ጉልህ ሚና አለው ብለዋል። ኢትዮጵያ በውኃ ሀብት አስተዳደርና በተፋሰስ ልማት ስራዎች እየከናወነች ያለው ሥራ ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን በመግለጽ። በሌላ በኩል ሚኒስቴሩ በተፋሰስ ልማትና በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ስራዎች ተስፋ ሰጪ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል። ከውሃ ሀብት በተጨማሪ የኢነርጂ ሀብትን በአግባቡ መለየትና ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባም አንስተዋል።   በመድረኩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የፌዴራልና የክልሎች እንዲሁም ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የውሃ እና ኢነርጂ ቢሮ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል።
የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ጥቅምን በተግባር ስላየነው አጠናክረን እንቀጥላለን - አርሶአደሮች
Jan 22, 2026 189
አሶሳ፤ ጥር 14/2018 (ኢዜአ)፦ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ጥቅምን በተግባር በማየታቸው ተግባሩን አጠናክረው መቀጠላቸውን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የቡልድግሉ ወረዳ አርሶአደሮች ተናገሩ። በምዕራብ ወለጋ ዞን በ 487 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው የተፋሰስ ልማት የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሰረት ሆኗል- ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ   አርሶአደ ሂድር ኡስማን እንዳሉት፤ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ዘላቂ የመሬት አያያዝና አጠቃቀም እንዲኖር ከማድረግ በተጨማሪ የአካባቢውን የአየር ንብረት በማስተካከል ሚናው የጎላ ነው።   ወይዘሮ ማርታ ዋቅቶላ በበኩላቸው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ መሠራት ከጀመረ ወዲህ በጎርፍ የሚወሰደው ለም አፈር በመቀነሱ ምርታማነታቸው እንዲጨምርና የአካባቢው ሥነ-ምኅዳርም መጠበቁን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ፀጋን የማልማትና የመጠበቅ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ   ከዚህ በፊት የተከናወነው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ የተራቆቱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ በማድረግ በደን እንዲሸፈኑ ማስቻሉን ያስረዱት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጭ ቢራቱ ፉፋ ናቸው። ቀደም ሲል ከተሠራው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ተጠቃሚነታቸውን ገልጸው፤ በቀጣይም አካባቢን ጠብቆ ለትውልድ የማስተላለፍ ተግባር ስለሆነ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አርሶ አደሮቹ ለኢዜአ ገልጸዋል።   የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትልና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ አብዱልከሪም ሙሳ፤ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ የአካባቢውን ሥነ-ምኅዳር ይጠብቃል፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በደለል እንዳይሞላ ይረዳል ብለዋል። ስለዚህ አርሶአደሩ ተሳትፎውን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል። ዘንድሮው በክልሉ ከ57 ሺህ ሔክታር በላይ ማሳ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ለማከናወን መታቀዱን አውስተዋል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን በ 487 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ  ነው
Jan 22, 2026 134
ጊምቢ፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን በ487 ተፋሰሶች የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ በምዕራብ ወለጋ ዞን ግብርና በጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፍቅሩ ብርሃኑ እንዳሉት፣ በዞኑ በ487 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡   ባለፉት አመታት በዞኑ በተከናወኑ የተለያዩ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች በመጡ ተጨባጭ ለውጦች አርሶ አደሩን ተጠቃሚ በማድረጋቸው ለዘንድሮ ተፋሰስ ልማት ስራዎች በነቂስ ወጥተው እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል፡፡ በዞኑ ከ273 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የሚሸፍን የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ መካሄድ ጀምሯል በተለይም እየተከናወኑ ባሉ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የእርከን ስራና ቀደም ብለው የለሙ ተፋሰሶች ከእንስሳትና ከሰው ንክኪ ነጻ እንዲሆኑ ጥበቃ ይደረግለታል ብለዋል።   በዞኑ በላሎሳቢ፣ በመነስቡ፣ በጊምቢና ሆማ ወረዳዎች በእስካሁኑ እንቅስቃሴ በእርከን ስራ የተሻለ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በተፋሰስ ልማት መርሃ ግብር በተከናወኑት ስራዎች የተራቆቱ አካባቢዎች ወደ ልምላሜ መመለሳቸውን እና በዘንድሮው የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ምክንያት እንደሆናቸው የሚናገሩት ደግሞ አርሶ አደር አምቢሳ ጉዲና ናቸው፡፡   ልማቱ ቀደም ሲል በአፈር መሸርሸር ምክንያት ምርታማነት ቀንሶ የነበረው የእርሻ መሬታቸው አሁን ላይ ማገገሙን ጠቅሰዋል። አርሶ አደር ከኔሳ አሙማ በበኩላቸው፤ ባለፉት አመታት በተከናወኑት የእርከንና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች በአካባቢያቸው ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡   በመሆኑም በዘንድሮ የበጋ ወራት የእርከን ልማት ስራዎች ላይ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የኢጋድ የ40 ዓመታት ጉዞ፤ ከድርቅ አደጋ ምላሽ ሰጪነት እስከ ቀጣናዊ ትስስር ተዋናይነት
Jan 21, 2026 207
በሙሴ መለሰ ምስራቅ አፍሪካ በአፍሪካ አህጉር በየጊዜው ከፍተኛ ለውጥ የሚያስተናግድ እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ቀጣና ነው። ከ300 ሚሊየን በላይ ህዝብ የሚኖርበት ይህ ቀጣና ከፍተኛ የሰው ሀብት ያለው ሲሆን ፈጣን የወጣት ህዝብ እድገት እና የገበያ ተደራሽነት መስፋት እየታየበት ይገኛል። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የምስራቅ አፍሪካ አጠቃላይ ዓመታዊ ጥቅል ምርት(ጂዲፒ) እ.አ.አ በ2025 598 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር መድረሱን ገልጿል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ያሉ ሀገራት የሚገኙበት ቀጣና ነው ምስራቅ አፍሪካ። ምስራቅ አፍሪካ ግብርና፣ ቁም እንስሳት፣ ኢነርጂ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ንግድ፣ ትራንስፖርት፣ የኢኮኖሚ ኮሪደሮች እና በፍጥነት እያደገ የመጣው ዲጂታል ኢኮኖሚ እምቅ የኢኮኖሚ አቅሞቿ ናቸው። ከመልክዐ ምድራዊ አቀማመጥ አንጻርም የኢትዮጵያ ከፍታማ ስፍራዎች፣ የታላላቅ ሀይቆች ተፋሰስ እና የአፍሪካ ቀንድ ዝቅተኛ ቦታዎች ይጠቀሳሉ። ከቀይ ባህር እስከ ህንድ ውቅያኖስ ምስራቅ አፍሪካን የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የዓለም የማሪታይም ንግድ መተላለፊያ መስመሮች ይገናኙባታል።   ይህ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ ምስራቅ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ንግድ፣ ሎጂስቲክስ እና ጂኦ ፖለቲካ ውስጥ ያላትን ሚና አሳድጓል። ቀጣናው ለመረጋገት እና ለትብብር ያለው ጠቀሜታም በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ለብዙ ክፍለ ዘመናት በምስራቅ አፍሪካ የሚገኙ የተለያዩ ማህበረሰቦች በንግድ፣ በፍልሰት እና የባህል ትስስር ተጋምደዋል። በዘመናዊው ዓለም ይህ ታሪካዊ ትስስር ለቀጣናዊ ትስስር ጠንካራ አስተዋጽኦ ያለው ነው። በሀገራት በጋራ የሚገነቡ መሰረተ ልማቶች፣ የተሳናሰኑ ፖሊሲዎች እና የሰዎችና እቃዎች ነጻ ዝውውር የኢኮኖሚ እድገት እና አጠቃላይ ልማትን የሚያሳልጥ ነው። ቀጣናዊ ትስስር የተበታተነ ገበያ ወደ አንድ ማዕቀፍ ለማምጣት፣ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ዜጎች በተለይም ወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አኳያ አስተዋጽኦወ ቁልፍ ነው። ምስራቅ አፍሪካ እንደ እድሎቹ ሁሉ በርካታ ፈተናዎች ያሉበት ቀጣና ነው። በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚፈጠረው ድርቅ እና ጎርፍ፣ ግጭት፣ መፈናቀል እና የልማት ተደራሽነት ፍትሃዊ አለመሆን በዋናነት የሚነሱ ጉዳዮች ናቸው። እነዚህ ድንበር ተሻጋሪ ፈተናዎች ከተናጠል ይልቅ የጋራ የተግባር ምላሽ ይፈልጋሉ። ፈተናዎችን ከግምት በማስገባት በቀጣናው በተደጋጋሚ ለሚከሰተው ድርቅ እና የከባቢ አየር ችግር የተቀናጀ ምላሽ መስጠት የሚያስችለው ተቋማዊ ማዕቀፍ ከ40 ዓመታት በፊት ወደ ስራ ገባ። ይህ ተቋም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ነው። የኢጋድ መቋቋም እርሾ በወቅቱ በቀጣናው ያጋጥሙ የነበሩ ቀውሶች ናቸው። እ.አ.አ በ1980ዎቹ መጀመሪያ በቀጣናው የነበረው ድርቅ እና ረሃብ የብዙ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈ ሲሆን ይህም ቀጣናው ለአየር ንብረት ለውጥ ያለውን ተጋላጭነት በግልጽ የሚያሳይ ነው። አደጋዎቹ ድንበር ተሻጋሪ በመሆናቸው የተቀናጀ የጋራ ምላሽ የሚፈልጉ ናቸው።   ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን እና ዩጋንዳ ለአንገብጋቢው ቀጣናዊ ጉዳይ ምላሽ በመስጠት ኢጋድን እ.አ.አ በ1986 አቋቋሙ። ኢጋድ በወቅቱ ሲቋቋም ዋነኛ የስራ ድርሻው የነበረው ድርቅ፣ በረሃማነት እና ሁለቱ የሚያደርሷቸውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽእኖዎችን ለመከላከል የሚደረጉ ቀጣናዊ ጥረቶችን ማስተባበር ነው። ይሁንና የከባቢ አየር ፈተናዎቹ ከፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ግጭት እና ካለመልማት ጋር ጥልቅ ቁርኝት ያላቸው መሆኑ አድማሱ የሰፋ ግብ ያለው ቀጣናዊ ተቋምን መፍጠር እንደሚያስፈልግ በወቅቱ ይነሳ ነበር። በዚሁ መሰረት ኢጋድ እ.አ.አ በ1996 በድጋሚ አደረጃጀቱ ተስተካክሎና የስራ ድርሻው ሰፍቶ እንደገና ተቋቋመ። ከድርቅ እና ከባቢ አየር ጉዳዮች በመሻገር ኢጋድ ሰላም እና ደህንነትን ማረጋገጥ፣ የኢኮኖሚ ትብብር እና ትስስር እንዲሁም ቀጣናዊ ትስስርን ማጎልበት የተቋሙ ቁልፍ የትኩረት መስኮች ሆነዋል። የኢጋድ ዋና መቀመጫ ጅቡቲ ነው። የሰፋው የስራ ድርሻ ኢጋድን በአፍሪካ ቀንድ የምክክር፣ የውይይት እና የተቀናጀ ልማት የጋራ ማዕቀፍ እንዲሆን አድርጎታል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) እ.አ.አ በ2026 የተመሰረተበትን 40ኛ ዓመት እንደሚያከብር ከሰሞኑ አስታውቋል። ኢጋድ በአራት አስርት ዓመታት ውስጥ በስኬት ደረጃ ሊነሱ የሚችሉ ተግባራትን አከናውኗል። ከሰላም እና ደህንነት አንጻር ኢጋድ በቀጣናው ውስብስብ የሚባሉ ግጭቶች በእርቅ እና በውይይት እንዲፈቱ አስተዋጽኦ አድርጓል። ለዓመታት በሱዳን ሲካሄድ የነበረውን የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲያበቃ እ.አ.አ በ2005 ሁሉን አቀፍ የሰላም ስምምነት እንዲፈረም በሰላም ሂደት ውስጥ የድርሻውን ተወጥቷል። ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ደቡብ ሱዳን በህዝበ ውሳኔ ራሷን የቻለች ሀገር ሆናለች። ኢጋድ በሶማሊያ የሰላም ጥረቶች ቁልፍ ተዋናይ ነበር። በሶማሊያ የፖለቲካ እርቅ እና መረጋጋት እንዲፈጠር ሲከናወኑ በነበሩ ስራዎች ላይ ተሳትፎ አድርጓል። ቀጣናዊ ተቋሙ ባለው የእርቅ የስራ ክፍል ግጭቶች እንዳይከሰቱና ከተከሰቱም እንዲፈቱ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣም ይገኛል። ከተቋቋመበት የስራ ድርሻ አኳያ ኢጋድ በምግብ ደህንነት፣ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አደጋ ስጋት አስተዳደር ላይ ሰፋፊ ተግባራትን አከናውኗል። ለአብነትም የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያና ትግበራ ማዕከል (ICPAC) የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓቶችን በማጠናከር፣ በአየር ትንበያዎች እና የፖሊሲ ድጋፎች አማካኝነት አባል ሀገራት ለድርቅ እና ጎርፍ አደጋዎች ምላሽ እንዲሰጡ የድርሻውን እየተወጣ ይገኛል። ይህም ቀጣናዊ የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽን ለማጠናከርና የመንግስታትን አቅም ከመገንባት አኳያ ትልቅ ድርሻ እንደተወጣ ማዕከሉ ይገልጻል። ከኢኮኖሚ ትብብር እና ቀጣናዊ ትስስር አኳያም ኢጋድ ድንበር ተሻጋሪ ንግድ እንዲያድግ፣ መሰረተ ልማት እንዲስፋፋና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እንዲጠናከሩ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በትራንስፖርት ኮሪደሮች፣ በአርብቶ አደሮች እንቅስቃሴዎችና ቀጣናዊ ገበያዎች ላይ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ በአባል ሀገራት እንዲተገበር ከማድረግ ባለፈ ድጋፉን እየሰጠ ነው። ኢጋድ በቀጣናው ለንግድ እና ለእንቅስቃሴ የሆኑ መሰናክሎች እንዲቀንሱ አስተዋጽኦ አድርጓል። ኢጋድ ከፍልሰተኞች ና ተፈናቃዮች ጋር ያሉ ችግሮች እንዲፈቱና ጉዳዩ ከፈተና ባለፈ የልማት እድል እንደሆነ በማንሳት ሁሉን አቀፍ እይታ እንዲፈጠር እየሰራ ይገኛል። በአራት አስርት ዓመታት ውስጥ ኢጋድ ተቋማዊ አቅሙን በማጠናከርና አጋርነቱን በማስፋት ረገድ የተለያዩ ስራዎችን አከናውኗል። ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ከሌሎች ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር እየሰራ ነው። ተቋሙ በቴክኒካዊ እና ፖለቲካዊ ደረጃዎች ለአባል ሀገራት ቋሚ የምክክር ማዕቀፍ ሆኖ እያገለገለ ሲሆን ይህም በሀገራት መካከል የጋራ መተማመንና የጋራ መግባባት እንዲኖር ያለው አስተዋጽኦ ወሳኝ የሚባል ነው። የኢጋድ የ40 ዓመታት ጉዞ በስኬቶች ብቻ የታጀበ አይደለም። ቀጣናዊ ተቋሙ ከፍተኛ ፈተናዎችም አጋጥመውታል። የመጀመሪያው በተደጋጋሚ ጊዜ የሚቀሰቀሱ እና ዘላቂ መቋጫ ያላገኙ ግጭቶችና የፖለቲካ አለመረጋጋቶች ናቸው። ጉዳዮቹ የኢጋድን የእርቀ ሰላም ጥረቶች ፈተና ውስጥ ከተውታል። አንዳንድ ጊዜ በአባል ሀገራት መካከል ያሉ መከፋፈሎች ኢጋድ ቆራጥ ውሳኔ እንዳይወስን ሲገድበው ታይቷል። የፋይናንስና ተቋማዊ አቅም ውስነነቶች የኢጋድ የተለያዩ ማዕቀፎች ትግበራ ላይ መስተጓጎሎችን ፈጥረዋል። ኢጋድ ከውጭ አጋሮች የሚያገኘው ፈንድ ከራስ ዘላቂ የፋይናንስ አቅርቦት ጋር ማመጣጠን አለመቻል የተቋሙን የዘላቂነት እና የባለቤትነት ጉዳይ ላይ ተጽእኖ አሳድረዋል። የፖለቲካ ተንታኞች ተቋሙ ከአባል ሀገራቱ የሚያገኝውን ጨምሮ ገቢ እና የፋይናንስ ቅሙን የሚያጠናክርባቸውን መንገዶች በሚገባ ማየት እንዳለበት ይመክራሉ። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ሌላኛው የኢጋድ ፈተና ነው። በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ደጋግመው የሚከሰቱ ድርቆች እና የጎርፍ አደጋዎች በተቋማዊ ምላሽና አቅም ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድረዋል። ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት መስፋፋትና መፈናቀል ጫናዎቹ ይበልጥ እንዲበረቱ አድርገዋል። ቀጣናዊ ስምምነቶችና የአሰራር ማዕቀፎችን ወደ ተጨባጭ የሀገራት ትግበራ የማሸጋገር ጉዳይም ትኩረት እንደሚያሻውም ይነሳል። የሀገራት የሚለያዩ የትኩረት መስኮች እና አቅሞች በቀጣናዊ ማዕቀፎች ሂደትና ትግበራ ላይ የራሳቸውን ተጽእኖ ያሳድራሉ። 40 ዓመታትን ያስቆጠረው ኢጋድ በምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ትብብር ያለውን ወሳኝ ጠቀሜታ የሚያሳይ ህያው ተቋማዊ ምስክር ነው። ለድርቅ እና ረሃብ ምላሽ ከመስጠት በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት፣ አንድነት እና ልማት ቁልፍ ተዋናይነት ተሸጋግሯል። አንድነት እና የፖለቲካ ቁርጠኝነትን በኢጋድ አባል ሀገራት መካከል ማጠናከር ለቀጣናዊ የተግባር ምላሽና ለተቋሙ ዘላቂ ውጤታማነት ወሳኝ የሚባሉ ጉዳዮች ናቸው። የአባል ሀገራት የጋራ አንድነት የተረጋገጠበት ኢጋድ ለቀውሶች ምላሽ ከመስጠት ባለፈ ለጋራ ፍላጎቶች መሳካት ያለው ሚናም ያድጋል። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ግንባታና ዘላቂ ልማት ላይ ቀጣይነት ባለው መልኩ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ የኢጋድ የትኩረት አጀንዳ ሊሆን ይገባል። የኢጋድ የሰላም እና መረጋጋት ጥረቶች በሁሉን አቀፍ አስተዳደር፣ በወጣቶችና ሴቶች የነቃ ተሳትፎ እንዲሁም በዘላቂ የሀገር ግንባታ አካሄዶች ሊደገፍ እንደሚገባ የፖለቲካ ባለሙያዎች ምክረ ሀሳባችውን ያስቀምጣሉ። የልማት ፍላጎት አለመሟላት እና የኑሮ ውድነትን ለግጭቶች አበይት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን ከስር መሰረቱ መፍታት ለዘላቂ መረጋጋት ወሳኝ ነው። ኢጋድ የተጣለበትን ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር እውን የማድረግ ኃላፊነቱን የበለጠ ለመወጣት የመሰረተ ልማት ትስስሮች ማጠናከር፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እውን ማድረግና በቀጣናው በፍጥነት እያደገ ለመጣው ዜጋ የስራ ፈጠራና እድሎችን የሚያሰፉ ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶችን የማስፋት ስራ ላይ አበክሮ መስራት ይኖርበታል። ፈተናዎች እንዳሉ ሆነው የኢጋድ የ40 ዓመታት ጉዞ የሚያሳየው አንድ ግልጽ ሀቅ አለ። ይህም እውነታ የምስራቅ አፍሪካ መጻኢ ጊዜ እርስ በእርስ መተሳሰርና በትብብር መቆም እንደሆነ ነው። የተቋቋመበትን አላማ ዳግም ቃል ኪዳኑን በማደስ በቁርጠኝነት መስራት ከቻለ፣ ተቋማዊ አቅሙን በሚገባ ካጎለበተ፣ በሀገራት መካከል አጋርነትና ትብብርን ካጠናከረና የዲጂታል ዘመን በሚገባ በመዋጀት ከሰራ ኢጋድ ቀጣዩ ትውልድ ሰላማዊ፣ አይበገሬናና የበለጸገ ቀጣና እንዲረከብ በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና መጫወቱን መቀጠል ይችላል።
የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ትብብራቸውን ለማጽናት ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Jan 14, 2026 193
አዲስ አበባ፤ ጥር 6/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን በባለብዙ ወገን መድረኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አያኖ ኩኒሚትሱ ጋር በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተወያይተዋል።   የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ትብብር እንዳላቸው አውስተው በጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም (ቲካድ) ማዕቀፍ ያላቸውን ግንኙነት አንስተዋል። በዮካሃማ በነሃሔ ወር 2017 ዓ.ም የተካሄደው ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም(ቲካድ) በሁለቱ ወገኖች አጋርነት ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው መሆኑን አመልክተዋል። ውይይቱ የሁለትዮሽ ትብብሩን የበለጠ ማጠናከርን ያለመ ነው። ጃፓን ለአፍሪካ የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (African CDC) እያደረገች ያለው ድጋፍ እንዲሁም የአፍሪካ ዘላቂ እድገት እና ትስስር ለሚደግፉ የመሰረተ ልማት ስራዎች እያፈሰሰች ያለው መዋዕለ ንዋይ እያደገ መምጣቱ ተመላክቷል። የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አያኖ ኩኒሚትሱ ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም (ቲካድ) በስኬት መካሄዱን አድንቀዋል። 10ኛው ቲካድ በአፍሪካ እንዲካሄድ ጃፓን ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ጋር በቅርበት ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን አመልክተዋል።   ሀገራቸው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና (AfCFTA) እና የአፍሪካ የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ፕሮግራም (ፒዳ) ጨምሮ የአፍሪካ ህብረት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ቁልፍ ኢኒሼቲቮች መደገፏን እንደምትቀጥል ገልጸዋል። በሌላ በኩል ሚኒስትር ዴኤታዋ በዓለም አስተዳደር ውስጥ እያደገ የመጣውን የአፍሪካ ሚና በማንሳት የአፍሪካ ህብረት በቡድን 20 ቋሚ አባል መሆኗ ትልቅ ሽግግር መሆኑን ተነግረዋል። ባለስልጣናቱ በአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን የከፍተኛ ደረጃ የምክክር መድረክ እና ቲካድ አማካኝነት ትብብራቸውን የበለጠ ለማጠናከር እና የባለብዙወገን ዲፕሎማሲ እንዲጸና በጋራ እንደሚሰሩ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን እ.አ.አ በ1993 አጋርነት መመስረታቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ። ሰላም እና ደህንነት፣ ኢኮኖሚ፣ ልማት፣ ንግድ፣ ጤና ፣ ግብርና፣ ቴክኖሎጂ እና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ከሁለቱ ወገኖች የትብብር መስኮች መካከል ይጠቀሳሉ።
ውኃ ለአፍሪካ የኅልውና ጉዳይ ነው - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Jan 12, 2026 289
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ ውኃ ሁሉንም ዘርፍ የሚነካ አህጉራዊ የኅልውና ጉዳይ መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የሕብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ስብሰባው"ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሐሳብ የሚደረግ ነው።   በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ፣ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት ትኩረቱን ያደረገው በውኃ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ውኃ በሁሉም አይነት እጅጉን ወሳኝ የሆነ ሀብት እና የኅልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ አህጉራዊ ግቦቹን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አስገንዝበዋል። በብራዚል ቤለም የተካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) ትኩረት ከተሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል አንዱ መሆኑንም አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በምታዘጋጀው 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ውኃ አንዱ አጀንዳ እንደሚሆንም ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማዘጋጀት በመመረጧ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ያሉ ሲሆን፤ ለጉባኤው ስኬታማነት ሕብረቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ሰላም እና ደኅንነት የአፍሪካ አንገብጋቢ አጀንዳ መሆኑን የገለጹት ሊቀ መንበሩ ሱዳን፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሊቢያን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ኢ-ሕገመንግሥታዊ ለውጦች አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው፤ ሀገራት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንዲያከብሩ አሳስበዋል። የአፍሪካ ሕብረት ተቋማዊ ሪፎርም እና ኢኮኖሚያዊ ትሥሥርን ጨምሮ ለአህጉራዊ አጀንዳዎች እየሠራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። አህጉራችን ፈተናዎች ቢኖሩባትም በጋራ ከቆምን እናልፋቸዋለን ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የዛሬው ስብስባ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን፤ የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ መሆኑ ይታወቃል።
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ይጀመራል
Jan 12, 2026 310
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚደረግ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣የሕብረቱ አባል አገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብስባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል አገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
ሐተታዎች
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 179
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ።   በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 631
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 570
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 793
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 615
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 567
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 1196
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3511
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3162
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2026
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7837
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6323
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 59858
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53868
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34495
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32046
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27384
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26297
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25833
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25672
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 59858
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53868
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34495
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32046
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ዕድሜ  ያልገደበው የልማት አርበኝነት 
Jan 14, 2026 265
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት ብርቱዎች ነገን በማሰብ ሁሌም ታትረው ይሰራሉ፤ ይደክማሉ፤ ይጥራሉ…ለቀጣዩ ትውልድም ጥሪት በማስቀመጥ አሻራቸውን ያኖራሉ። አገር የምትገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው። “አባት ያበጀው፤ ለልጅ ይበጀው” እንደሚባለው ልጆች ከአባቶቻቸው ያገኙትን ጥሪት በአዲስ እውቀትና አሰራር ለአገር እድገት በሚበጅ መልኩ አጠናክረው መጠቀማቸው አይቀርም። “ዕድሜ ጸጋ ነው” የሚለው አባባል አንዳንዴ በዕድሜ ብንገፋም ጠንክረን ከሰራን ብዙ ነገር እናያለን ከሚለው ጋር የተያያዘ ነው። በሰቆጣ ከተማም እድሜ ሳይገድባቸው በልማት ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ለዚህ ማሳያ ናቸው። የከተማዋ ነዋሪ የ67 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ አወቀ እና የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ዕድሜያቸው ቢገፋም ጠንክሮ ከተሰራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና ዕድሜ ጸጋ ሆኖ ብዙ ለውጥ ማየት እንደሚቻል ማሳያ ናቸው። ግለሰቦቹ ከዕድሜ ብዛት ጉልበቴ ደከመ፣ አይኔ ፈዘዘ፣ እጄም ተሳሰረ…ሳይሉ ጊዜያቸውን በደን፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ በማሳለፍ ለወጣቶች የልማት አርአያነት ያለው ተግባር እየፈጸሙ ነው። አቶ ብርሃኑ አወቀ በሰቆጣ ከተማ ዳርቻ የሚገኝ አለቱ ያገጠጠና የተራቆተ አካባቢን ከሌላ አካባቢ ለም አፈር በማምጣትና በመደልደል አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ደን በማልማት ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ነው።   ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከወጣሁ ጀምሮ ጠንክሬ በመስራት የምለወጥበትን ሥራ ማሰብ ስነበረብኝ፤ የቆሻሻ መጣያ ሆኖ ለዘመናት የቆየን ጭንጫ መሬት ጠርጌና ደልድዬ ማልማት ችያለሁ ይላሉ ወደኋላ መልስ ብለው የተነሱበትን ሁኔታ ሲያስታውሱ። ግማሽ ሄክታር በማይሞላ መሬት ላይ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ዘይቱና፣ ጌሾ፣ ቡና፣ ማንጎና አቮካዶ አልምተዋል። በተጨማሪም ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመንና ሽንኩርት በማምረት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ጥሪት አፍርተዋል።   ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ተግቶ መስራት ከተቻለ ሀብት ማፍራትና ህይወትንም መለወጥ እንደሚቻል የገለጹት አቶ ብርሀኑ፣ ወጣቱም ከእሳቸው የሥራ ትጋት በመማር በአካባቢው ያለውን ፀጋ ለይቶ በማልማት ሊጠቀም ይገባል ሲሉ ይመክራሉ። ሌላው የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ባለፉት 18 ዓመታት በተሰማሩበት የአትክልትና ደን ልማት ሥራ የአካባቢያቸውን ገጽታ ቀይረዋል። የዕድሜ ዘመናቸውን በውትድርናና በመንግስት ሠራተኝነት በማገልገል ሃገራዊ ግዳጃቸውን ሲወጡ ነው የቆዩት።   ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከተገለሉ በኋላም ቤት ውስጥ መቀመጥን አልመረጡት። አካፋና ዶማቸውን ይዘው ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ ጌሾ፣ ዘይቱና እና ማንጎ በማልማት ምርቱን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። በአካባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ለይተን ማልማት ከቻልን ድህነትን ማስወገድ የሚከብድ አይሆንም ያሉት አቶ ታደሰ፣ የተራቆተና በጎርፍ የተጎዳን መሬት በማልማት አካባቢውን ሳቢና ማራኪ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት። ወጣቱም ከእሳቸው አርአያነት ያለው ተግባር በመማር በአካባቢው እጁ ላይ ባለ ሀብት ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል በተግባር ማሳየት እንዳለበት መክረዋል።   የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ እንደገለጹት፤ በብሔረሰብ አስተዳደሩ 24ሺህ 847 አርሶ አደሮች በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተዋል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል ዕድሜ ሳይገድባቸው ወደ ልማት የገቡ አረጋዊያን እያከናወኑት ያለው የግብርና ልማት ሥራ ለወጣቱ ትልቅ ትምህርት እንደሚሆንም ተናግረዋል። ከእነሱ ልምድ በመውሰድ በዞኑ ወጣቶች፣ ሴቶችና አረጋዊያን በጓሮና ባላቸው መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲያለሙ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ይህም በዞኑ የሚስተዋለውን የስርዓተ ምግብ ችግር ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።
ከማላጋ እስከ አፍሪካ ዋንጫ፤ የሞሮኮው አዲስ እንቁ ብራሂም ዲያዝ
Jan 13, 2026 283
  የግል ክህሎት፣ ፈጣን አስተሳሰቡ እና በጠባብ ክፍተቶች ውስጥ ሰብሮ የመግባት አቅሙ ሙገሳ እንዲጎርፍለት አድርጓል። አንድ ለአንድ ሲገናኝ ተከላካዮችን በፈጣን አካላዊ ቅልጥፍና እና በድንገት አቅጣጫ በመቀየር የሚያልፍበት መንገድ እንዲሁም የመፍጠር አቅሙ የተመልካቾችን ቀልብ የሚይዝ ነው። የአማካይ እና የአጥቂ መስመርን በማገናኘት እና በአስገራሚ ሁኔታ አጭር ኳሶችን በማቀበልም የተዋጣለት ተጫዋች ነው ማለት ይቻላል። በቦታ አያያዙ የእግር ኳስ ልኅቀቱ ከፍተኛ ነው የሚል አድናቆት ከእግር ኳስ ባለሙያዎች አግኝቷል። ኳስን ሲያንከባልልም ለዐይን ይስባል። ከክህሎቱ እና ከማራኪ እንቅስቃሴው ባለፈ ወደ ኋላ እየመለሰ ተከላካዮችን ያግዛል፣ ኳስ ይነጥቃል። ይህ ተጫዋች የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ክስተት የሆነው የሞሮኮው ብራሂም ዲያዝ ነው። የ26 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ዲያዝ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አምስት ጨዋታዎችን አድርጎ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ነው። አዘጋጇ ሞሮኮ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ መክፈቻ ኮሞሮስን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የውድድሩን የመጀመሪያ ግብ አስቆጥሯል።   ብራሂም አብዱልቃድር ዲያዝ የተወለደው እ.አ.አ ኦገስት 3 ቀን 1999 በስፔን ማላጋ ግዛት ነው። እናቱ ስፔናዊ አባቱ ሞሮኳዊ ናቸው። ዲያዝ ያደገው በማላጋ ነው። እግር ኳስንም በአንዳሉሺያዊቷ ከተማ ሲጫወት ቆይቷል። በ16 ዓመቱ ካደገበት ማላጋ በመውጣት እ.አ.አ በ2015 ወደ ማንችስተር ሲቲ ወጣት አካዳሚ በ200 ሺህ ፓውንድ ወጪ ተዘዋወረ። ዲያዝ እ.አ.አ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2016 በካራባኦ ካፕ (በቀድሞ አጠራሩ ሊግ ካፕ) ማንችስተር ሲቲ ከስዋንሲ ሲቲ ባደረገው ጨዋታ በ80ኛው ደቂቃ በኬሌቺ ኢናቺዩ ተቀይሮ በመግባት ለውኃ ሰማያዊዎቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያውን ጨዋታ ካደረገ ከሶስት ቀናት በኋላ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለሶስት ዓመታት የሚያቆየውን ፕሮፌሽናል ኮንትራት ተፈራርሟል። እ.አ.አ ኖቬምበር 21 ቀን 2017 ማንችስተር ሲቲ ከፌይኖርድ ሮተርዳም ጋር ባደረገው የሻምፒዮናስ ሊግ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል። በወቅቱ ብራሂም ስተርሊን መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ሰዓት ላይ ነበር ተቀይሮ የገባው። ዲያዝ በውኃ ሰማያዊዎቹ ማልያ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የተጫወተው እ.አ.አ ዲሴምበር 19 ቀን 2017 ነው። ማንችስተር ሲቲ ከሌስተር ሲቲ በካራባኦ ካፕ ጨዋታ ላይ ለ88 ደቂቃዎች ተሰልፎ ተጫውቷል።   እ.አ.አ ጃንዋሪ 20 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን 3 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በወቅቱ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ያነሳ ሲሆን፤ በውድድር ዓመቱ አራት ጨዋታዎች ላይ ብቻ ተሳትፎ ያደረገው ብራሂም ዲይዝ የሜዳሊያ ሽልማት አግኝቷል። እ.አ.አ ኦገስት 5 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ቼልሲን 2 ለ 0 ባሸነፈበት የኮሙዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ላይ በፊል ፎደን ተቀይሮ በመግባት ለ15 ደቂቃዎች ተጫውቷል። ዲያዝ እ.አ.አ 2018/19 ማብቂያ ላይ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የመጀመሪያ ግቦቹን ለሲቲ አስቆጥሯል። በማንችስተር ሲቲ ያለው ውል እ.አ.አ 2019 ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት ስሙ ከዝውውር ጋር በስፋት ይነሳ ነበር። ዲያዝ እ.አ.አ ጥር 2019 በ17 ሚሊዮን ዩሮ ከማንችስተር ሲቲ ወደ ሪያል ማድሪድ ተዘዋወረ። ለስድስት ዓመታት የሚያቆየውን ውልም ፈርሟል። የክንፍ ተጫዋቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን በነጮቹ ማልያ ያደረገው እ.አ.አ ጥር 9 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ ሌጋኔን በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ 3 ለ 0 ባሸነፈበት ወቅት ነው። ከአራት ቀናት በኋላ በስፔን ላሊጋ ሪያል ማድሪድ ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ ተቀይሮ በመግባት በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያ ግቡን ለማስቆጠር ሶስት ወራትን ጠብቋል። እ.አ.አ ግንቦት 12 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ በላሊጋው በሪያል ሶሲዬዳድ 3 ለ 1 ሲሸነፍ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በወቅቱ ዲያዝ ስድስት ጨዋታዎች ላይ በላሊጋው የተጫወተ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ዓመቱ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ሪያል ማድሪድ እ.አ.አ በ2021/21 የውድድር ዓመት ብራሂም ዲያዝ ወደ ኤሲ ሚላን በውሰት ማምራቱን ይፋ አደረገ። ዲያዝ ሚላን እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2020 ክሮቶኔን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ የመጀመሪያ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ ግንቦት 2021 ኤሲ ሚላን ጁቬንቱስን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ያስቆጠረው ግብም ተጠቃሽ ነው። ዲያዝ በኤሲ ሚላን የውሰት ውሉ ሲያበቃ በድጋሚ ለሁለት ዓመታት በውሰት የሚቆይበት ስምምነት ሪያል ማድሪድ ከጣልያኑ ክለብ ጋር የተፈራረመ ሲሆን፤ ውሉ ሚላን ተጫዋቹን የማቆየት መብት ሰጥቶታል። እ.አ.አ መስከረም 15 ቀን 2021 ኤሲ ሚላን በሻምፒዮንስ ሊጉ የ3 ለ 2 ሽንፈት ሲያስተናግድ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ግቡን አስቆጥሯል። በ2023 ኤሲ ሚላን ቶተንሃም ሆትስፐርስን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ 1 ለ 0 ሲያሽንፍ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023 ሰኔ ወር ላይ ሪያል ማድሪድ ዲያዝ ከኤሲ ሚላን የሶስት ዓመታት የውሰት ቆይታ በኋላ ወደ ክለቡ መመለሱን አሳውቋል። ተጫዋቹ በኤሲ ሚላን ቆይታው 91 ጨዋታዎችን አድርጎ 13 ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ዲያዝ ወደ ሪያል ማድሪድ ከተመለሰ በኋላ ኮንትራቱን እስከ 2027 አራዝሟል። እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2023 ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ሪያል ማድሪድ ላስ ፓልማስን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ አስቆጥሯል።   የክንፍ መስመር ተጫዋቹ ሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥ እና በአውሮፓ መድረክ በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ላይ ግብ በማስቆጠር እና ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ዲያዝ እስከ አሁን ለሪያል ማድሪድ ባደረጋቸው 129 ጨዋታዎች 20 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከነዚህም ውስጥ 13ቱ በላሊጋው ያስቆጠራቸው ናቸው። ከክለብ ወጣ ስንል የተጫዋቹን የብሔራዊ ቡድን ቆይታ እናገኛለን። ዲያዝ በታዳጊነቱ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ለስፔን ወጣት ቡድኖች ተጫውቷል። እ.አ.አ በ2016/17 የውድድር ዘመን ለስፔን ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በ16 ዓመቱ ተሰልፎ መጫወት ችሏል። በተለይም አዘርባጃን እ.አ.አ በ2017 ባዘጋጀችው 15ኛው የአውሮፓ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ላይ ያሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆት አስችሮታል። በዚያ ቀጥለው በነበሩ ዓመታትም ለስፔን ከ19 እና ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቷል። ብራሂም ዲያዝ በስፔን ታዳጊና ወጣት ቡድኖች ላይ በአጠቃላይ 28 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። የስፔን ታዋቂ የስፖርት ጋዜጣ ማርካ እ.አ.አ ጥር 23 ቀን 2023 ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን መጫወት ማቀዱን የሚመለከት ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ከዜግነቱ ጋር በተያያዘ ያሉ አንዳንድ የአስተደዳር ጉዳዮች በወቅቱ መፍትሄ አግኝተዋል። ይሁንና ኮትዲቯር እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሞሮኮው አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከተጫዋቹ ጋር በተደረገ የቅድሚያ ስምምነት ለተጫዋቹ ጥሪ አልተደረገለትም። ዲያዝ እ.አ.አ መጋቢት 10 ቀን 2024 ለሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሀገሪቷ ብሔራዊ መጫወት እንደሚፈልግ በይፋ ማሳወቁን ማርካ በወቅቱ ዘግቧል። ጥያቄውም ተቀባይነት አገኘ። በወቅቱ የሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ብሔራዊ ቡድኑ ከአንጎላ እና ሞሪታኒያ ጋር ለነበረበት የወዳጅነት ጨዋታ ለዲያዝ ጥሪ አድርገውለታል። እ.አ.አ መጋቢት 22 ቀን 2024 ሞሮኮ አንጎላን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። እ.አ.አ ጥቅምት 6 ቀን 2024 ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከጋቦን ጋር ባደረገችው ጨዋታ 4 ለ 1 ስታሸንፍ የመጀመሪያ ግቡን ለሞሮኮ ማስቆጠር ቻለ። እ.አ.አ ሕዳር 15 ቀን 2024 ሞሮኮ በማጣሪያው ጋቦንን 5 ለ 1 ስትረታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። ከሶስት ቀናት በኋላ ሞሮኮ ከሌሴቶ ጋር ባደረገችው የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ 7 ለ 0 ስታሸንፍ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር በሀገሩ ማልያ የመጀመሪያ ሀትሪኩን ሰርቷል። እ.አ.አ ጥቅምት 2025 ሞሮኮ ራባት ላይ ኮንጎ ሪፐብሊክን 1 ለ 0 በማሸነፍ በስፔን ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተይዞ የነበረውን 15 ተከታታይ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ክብረ ወሰን በመስበር ወደ 16 ማድረስ ችላለች። በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ ላይ ዲያዝ ተሰልፎ ተጫውቷል። የሞሮኮ ተከታታይ የማሸነፍ ጉዞ 19 ጨዋታዎች ደርሶ የነበረ ሲሆን በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከማሊ ጋር አንድ አቻ ስትለያይ አብቅቷል።   ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማጣሪያ ብታልፍም አስቀድማ ውድድሩን እንድታዘጋጅ እድል አግኝታ የነበረው ጊኒ በዝግጅት ማነስ ምክንያት በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ከሁለት ዓመት በፊት አዘጋጅነቷ ተነጥቆ ለሞሮኮ ተሰጥቷል። ሞሮኮ የዘንድሮውን ውድድር በደማቅ ሁኔታ እያካሄደች ትገኛለች። በውድድሩ ላይ ጎልተው ከታዩ ተጫዋቾች መካከል ብራሂም ዲያዝ ተጠቃሽ ነው። በአፍሪካ ዋንጫው እስከ አሁን ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። በተሰለፈባቸው በእያንዳዱ ጨዋታዎች ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን በአምስት የአፍሪካ ዋንጫ ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። ሞሮኮ በሩብ ፍጻሜው ማሊን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሯል። ሀገሩ ወደ ግማሽ ፍጻሜ እንድታልፍ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱንም እየመራ ይገኛል። ሞሮኮ በዚሁ ግስጋሴዋ ከቀጠለች ዲያዝ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና ኮከብ ተጫዋች የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። ሞሮኮ በግማሽ ፍጻሜው ከናይጄሪያ ጋር ረቡዕ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ታደርጋለች። ዲያዝ በዚህ ጨዋታ ላይ ልዩነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። አንዳንድ የእግር ኳስ ተንታኞች ብራሂም ዲያዝ እ.አ.አ በ2026 ወጥነት ያለው ብቃት ማሳየት ከቻለ የአፍሪካ ኮከብ ተጫዋችነት ሽልማቱን የሚወስድበት የለም እያሉ ይገኛሉ። ሞሮኳውያን በተጫዋቹ ፍቅር ልባቸው ከንፏል። በየጨዋታው ዲያዝ ዲያዝ እያሉ ከፍተኛ ድጋፍ እና ሙገሳ እየሰጡት ይገኛሉ። እሱም በድንቅ ብቃቱ ምላሽ እየሰጣቸው ነው። በተወለደበት ማላጋ ከተማ የጀመረው የእግር ኳስ ሕይወት በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የበለጠ አብቧል። የሞሮኮው አዲሱ ኮከብ ብራሂም ዲያዝ ቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወት በስኬት እና በድል የደመቀ እንደሚሆን ከአሁኑ ድንቅ ብቃቱ ተነስቶ መናገር ይቻላል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም