ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ለዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች
Jun 24, 2026 50
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሚጀመረው ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። ለዋናው ሀገራዊ ምክክሩ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች 1- የሀገር ግንባታ 2 -የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት 3 -የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬደዋ 4- የሃይማኖት ጉዳዮች 5- የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች 6 -ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች 7 -ሙስናና መልካም አስተዳደር 8 -ሰላም ግንባታ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ለመምህራን ልማት ትኩረት ተሰጥቷል
Jun 24, 2026 69
አርባ ምንጭ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚከናወኑ ተግባራት ለመምህራን ልማት ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው "በቅቶ ማብቃት ልቆ ማላቅ" በሚል መሪ ሃሳብ ለቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራን የአሠልጣኞች ስልጠና በአርባምንጭ ከተማ እየሰጠ ነው። የቢሮ ሃላፊው አብዮት ደምሴ ስልጠናው ዛሬ ሲጀመር እንደገለጹት በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሰው ሀይል ልማትና ግብአት አቅርቦት ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። ለዚህም ሀገር አቀፍ የትምህርት ፍኖተ ካርታውን በመተግበር የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ላይ ይበልጥ ለመስራት የመምህራን አቅም ማጎልበት ላይ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል። ዛሬ የተጀመረው የመምህራን የአሠልጣኞች ስልጠናም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑን ጠቁመዋል። ስልጠናው የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራንን አቅም በማጎልበት ህጻናትን በአሳታፊ ዘዴ እና በተግባራዊ እንቅስቃሴዎች የማስተማር ክህሎትን ለማዳበር አጋዥ መሆኑን አስታውቀዋል ። የቢሮው ምክትልና የመምህራን ትምህርት አመራር ልማት ዘርፍ ሃላፊ ታምራት ይገዙ (ዶ/ር) በበኩላቸው ትምህርት ለሀገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት መሰረት በመሆኑ ዘርፉን በእውቀት መምራት ይገባል ብለዋል ። ለዚህም የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራን የሙያ ብቃት ማጎልበቻ እና የደረጃ ማሟያ ስልጠና በየጊዜው ከመስጠትም በላይ መምህራን የትምህርት ደረጃቸውን እንዲያሻሽሉ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። ስልጠናው በቅቶ የሚያበቃና ልቆ የሚያልቅ መምህራንን በማፍራት ብቁ ትውልድ ለመገንባት ወሳኝ ነው ያሉት ደግሞ የአርባምንጭ ትምህርት ኮሌጅ ዲን እንግዳ እንድሪያስ (ዶ/ር) ናቸው። የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የህፃናትን የመማር ፍላጎት፣ ክህሎትና ስብዕና መሠረት አድርጎ መስራት አስገዳጅ መሆኑን አስረድተዋል ። ለዚህም ለአመቻች መምህራን የሙያ ብቃትን ማሳደግና ግብአትን ማሟላትን ይጠይቃል ብለዋል። የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ሀገርና ትውልድ ለመገንባት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ መጠናከር እንደሚገባውም አክለዋል።
ለዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስምንት አጀንዳዎች ተለይተዋል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Jun 24, 2026 147
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ለዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስምንት አጀንዳዎች መለየታቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ እንደሚካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል። በዛሬው እለትም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። በመርሀ ግብር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያን ጨምሮ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፥ ኮሚሽኑ ሁሉን አቀፍ ሂደትን በመከተል የተዋጣ ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል። በዚህም ስምንት ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው አጀንዳዎች ተለይተው ለዋናው የምክክር ጉባኤ መለየታቸውን ጠቁመዋል። ይፋ የተደረጉት ስምንቱ አጀንዳዎች የተቀረጹት ራሰን በቻለ ግልጽ ሥርዓተ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽኑ ላለፉት አራት ዓመታት ሰፊ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል፤ በተለያዩ ምዕራፎች ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል አሳታፊና አካታች የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሥራ ተሰርቷል። በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶችን በሰለጠነ ምክክር ለመፍታትና ሀገራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል ምኅዳር ተፈጥሯል። በኢትዮጵያ በሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮችና በውጭ ዓለማት ከሚኖሩ ዜጎች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ ተካሂዷል። የሀገራዊ ምክክሩ የእስካሁን ሂደትም ግልጽ፣ ገለልተኛ፣ አካታችና አሳታፊነቱን ጠብቆ የተካሄደ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሕዝባዊ ውይይቶች አጀንዳዎችን ያሰባሰበበት የእስካሁኑ የምክክር ሂደት ቁልፍ ባሕርያት
Jun 24, 2026 192
ባለድርሻ አካላት እንደሀገር ያልተግባባንባቸውን እጅግ መሠረታዊ የሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች በውይይት በማዳበር ለኮሚሽኑ ማስረከባቸው፤ የብዙ ባለድርሻ አካላት ሕመሞች፣ ሥጋቶች፣ ምኞቶች እና ተስፋዎች በአጀንዳ መልክ መቅረባቸው፤ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለምክክሩ ሂደት የሚጠቅሙ እጅግ በርካታ ግብዓቶችን መሰብሰቡ፤ በአንፃራዊነት የተሳታፊዎችን ምቾት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለተሳታፊዎች ቅርብ ናቸው ተብለው በሚታሰቡ ቦታዎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት መከናወኑ፤ በሕዝባዊ ውይይት አጀንዳን የመሰብሰብ ሥራ ሁለት ዓመታትን ፈጅቷል፤ በአጠቃላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔው መካሄድ እንደ ቅድመ ሁኔታ በማገልገል የራሱን ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ምክክር
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡን ወሳኝነት በግልጽ አረጋግጧል - የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Jun 24, 2026 245
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡን ወሳኝነት በግልጽ ያረጋገጠና ለሁሉም አካላት ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ ነው ሲል የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ። ምክር ቤቱ ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን የሕዝብ ድምጽ አግኝቶ ማሸነፉን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላልፏል። በመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክቱም፤ የክልላችንንና የሀገራችንን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ለመቅረፍ በትብብር፣ በፉክክርና በአንድነት መርኅ ላይ በመንተራስ ከመንግሥት እና ከገዥው ብልጽግና ፓርቲ ስሠራ ቆይቻለሁ ብሏል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫም በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩሉን መሥራቱን ጠቁሞ፤ የፓርቲዎቻችንን ፕሮግራም በተለያዩ አመራጮች ለሕዝብ በማቅረብ ለመወዳደር የቻልንበት ጊዜ ነበር ነው ያለው፡፡ አጠቃላይ የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን የሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ርብርብ ከፍተኛ እንደነበር አውስቶ፤ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላትም ውጤቱን ተቀብለው ለሕዝቡ ውሳኔም ተገዥ መሆናቸውን ለኢዜአ በላከው መረጃ አረጋግጧል። በዚህም መሠረት፤ ምርጫው በሰላም ተጠናቆ ሀገራችን ስላሸነፈች ለመላው ሕዝባችን እንኳን ደስ አላቸሁ ለማለት እንወዳለን ብሏል የጋራ ምክር ቤቱ። የምርጫው ሂደትና ውጤቱም ዴሞከራሲያዊና የሕዝብን ወሳኝነት ያረጋገጠ በመሆኑ የሕዝቡን ድምጽ በጸጋ እንቀበላለን ሲልም አስታውቋል። በዚህ ታሪካዊ የምርጫ ሂደት ውስጥ ለተሳተፉት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ለሁሉም ባለድርሻ አካላትም ምክር ቤቱ ምሥጋና አቅርቧል። በመጨረሻም ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን የሕዝብ ድምጽ አግኝቶ ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባረጋገጠው መሠረት፤ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለብልጽግና ፓርቲ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን በቀጣይ ክልላዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ ነን ሲል አረጋግጧል። በአጠቃላይ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡን ወሳኝነት በግልጽ ያረጋገጠና ለሁሉም አካላት ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ መሆኑንም ነው ያስታወቀው። በተጨማሪም ለሀገራችን የዴሞከራሲ ምኅዳር መስፋት ዐሻራ ጥሎ ያለፈ በመሆኑ፤ ሁሉም አካላት ይህንን ጅምር ሂደት ወደ ከፍተኛ ደረጃ ለማድረስ መሥራትና ከምርጫ ማግስት ጀምሮ ፊታችንን ወደ ልማትና ሰላም ግንባታ በማዞር በሁሉም ዘርፍ ለውጥ ለማምጣት መትጋት ይኖርብናል ነው ያለው፡፡ ብልጽግና ፓርቲም ሕዝቡ የሰጠውን አደራ በጥንቃቄ በመያዝ የሕዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ ሌት ተቀን ተግቶ እንዲሠራ ጠይቋል።
ፖለቲካ
ለዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች
Jun 24, 2026 50
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሚጀመረው ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። ለዋናው ሀገራዊ ምክክሩ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች 1- የሀገር ግንባታ 2 -የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት 3 -የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬደዋ 4- የሃይማኖት ጉዳዮች 5- የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች 6 -ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች 7 -ሙስናና መልካም አስተዳደር 8 -ሰላም ግንባታ
ለዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስምንት አጀንዳዎች ተለይተዋል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Jun 24, 2026 147
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ለዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስምንት አጀንዳዎች መለየታቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ እንደሚካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል። በዛሬው እለትም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። በመርሀ ግብር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያን ጨምሮ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፥ ኮሚሽኑ ሁሉን አቀፍ ሂደትን በመከተል የተዋጣ ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል። በዚህም ስምንት ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው አጀንዳዎች ተለይተው ለዋናው የምክክር ጉባኤ መለየታቸውን ጠቁመዋል። ይፋ የተደረጉት ስምንቱ አጀንዳዎች የተቀረጹት ራሰን በቻለ ግልጽ ሥርዓተ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽኑ ላለፉት አራት ዓመታት ሰፊ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል፤ በተለያዩ ምዕራፎች ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል አሳታፊና አካታች የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሥራ ተሰርቷል። በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶችን በሰለጠነ ምክክር ለመፍታትና ሀገራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል ምኅዳር ተፈጥሯል። በኢትዮጵያ በሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮችና በውጭ ዓለማት ከሚኖሩ ዜጎች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ ተካሂዷል። የሀገራዊ ምክክሩ የእስካሁን ሂደትም ግልጽ፣ ገለልተኛ፣ አካታችና አሳታፊነቱን ጠብቆ የተካሄደ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሕዝባዊ ውይይቶች አጀንዳዎችን ያሰባሰበበት የእስካሁኑ የምክክር ሂደት ቁልፍ ባሕርያት
Jun 24, 2026 192
ባለድርሻ አካላት እንደሀገር ያልተግባባንባቸውን እጅግ መሠረታዊ የሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች በውይይት በማዳበር ለኮሚሽኑ ማስረከባቸው፤ የብዙ ባለድርሻ አካላት ሕመሞች፣ ሥጋቶች፣ ምኞቶች እና ተስፋዎች በአጀንዳ መልክ መቅረባቸው፤ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለምክክሩ ሂደት የሚጠቅሙ እጅግ በርካታ ግብዓቶችን መሰብሰቡ፤ በአንፃራዊነት የተሳታፊዎችን ምቾት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለተሳታፊዎች ቅርብ ናቸው ተብለው በሚታሰቡ ቦታዎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት መከናወኑ፤ በሕዝባዊ ውይይት አጀንዳን የመሰብሰብ ሥራ ሁለት ዓመታትን ፈጅቷል፤ በአጠቃላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔው መካሄድ እንደ ቅድመ ሁኔታ በማገልገል የራሱን ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ምክክር
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡን ወሳኝነት በግልጽ አረጋግጧል - የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Jun 24, 2026 245
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡን ወሳኝነት በግልጽ ያረጋገጠና ለሁሉም አካላት ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ ነው ሲል የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ። ምክር ቤቱ ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን የሕዝብ ድምጽ አግኝቶ ማሸነፉን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላልፏል። በመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክቱም፤ የክልላችንንና የሀገራችንን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ለመቅረፍ በትብብር፣ በፉክክርና በአንድነት መርኅ ላይ በመንተራስ ከመንግሥት እና ከገዥው ብልጽግና ፓርቲ ስሠራ ቆይቻለሁ ብሏል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫም በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩሉን መሥራቱን ጠቁሞ፤ የፓርቲዎቻችንን ፕሮግራም በተለያዩ አመራጮች ለሕዝብ በማቅረብ ለመወዳደር የቻልንበት ጊዜ ነበር ነው ያለው፡፡ አጠቃላይ የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን የሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ርብርብ ከፍተኛ እንደነበር አውስቶ፤ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላትም ውጤቱን ተቀብለው ለሕዝቡ ውሳኔም ተገዥ መሆናቸውን ለኢዜአ በላከው መረጃ አረጋግጧል። በዚህም መሠረት፤ ምርጫው በሰላም ተጠናቆ ሀገራችን ስላሸነፈች ለመላው ሕዝባችን እንኳን ደስ አላቸሁ ለማለት እንወዳለን ብሏል የጋራ ምክር ቤቱ። የምርጫው ሂደትና ውጤቱም ዴሞከራሲያዊና የሕዝብን ወሳኝነት ያረጋገጠ በመሆኑ የሕዝቡን ድምጽ በጸጋ እንቀበላለን ሲልም አስታውቋል። በዚህ ታሪካዊ የምርጫ ሂደት ውስጥ ለተሳተፉት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ለሁሉም ባለድርሻ አካላትም ምክር ቤቱ ምሥጋና አቅርቧል። በመጨረሻም ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን የሕዝብ ድምጽ አግኝቶ ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባረጋገጠው መሠረት፤ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለብልጽግና ፓርቲ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን በቀጣይ ክልላዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ ነን ሲል አረጋግጧል። በአጠቃላይ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡን ወሳኝነት በግልጽ ያረጋገጠና ለሁሉም አካላት ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ መሆኑንም ነው ያስታወቀው። በተጨማሪም ለሀገራችን የዴሞከራሲ ምኅዳር መስፋት ዐሻራ ጥሎ ያለፈ በመሆኑ፤ ሁሉም አካላት ይህንን ጅምር ሂደት ወደ ከፍተኛ ደረጃ ለማድረስ መሥራትና ከምርጫ ማግስት ጀምሮ ፊታችንን ወደ ልማትና ሰላም ግንባታ በማዞር በሁሉም ዘርፍ ለውጥ ለማምጣት መትጋት ይኖርብናል ነው ያለው፡፡ ብልጽግና ፓርቲም ሕዝቡ የሰጠውን አደራ በጥንቃቄ በመያዝ የሕዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ ሌት ተቀን ተግቶ እንዲሠራ ጠይቋል።
ሰላማዊና የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት ኢትዮጵያና ብሩንዲ በጋራ ይቆማሉ-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jun 24, 2026 611
አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያና ብሩንዲ ሰላማዊና የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት ባላቸው የጋራ ቁርጠኝነት ዙሪያ አብረው እንደሚቆሙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ በሀገራቸው እና በአፍሪካ ህብረት ስም ያስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ትልቅ ብርታትን የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ብሩንዲ በጥልቅ የወንድማማችነት ትስስር፣እንዲሁም ሰላማዊና የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት ባላቸው የጋራ ቁርጠኝነት ዙሪያ አብረው ይቆማሉ ብለዋል። ለሁለቱ ሀገራት ወዳጅነት ትልቅ ዋጋ እንደሚሰጡ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሕዝቦቻችንና የአፍሪካን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጠውን ይህንን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ኢትዮጵያ ዝግጁ መሆኗን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ ከህንድ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ትሻለች-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jun 24, 2026 493
አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያ ከህንድ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማሳደግ እንደምትፈልግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሞዲ ያገኙትን ታሪካዊ የሕዝብ ውክልና የአለማችን ትልቁ ዲሞክራሲ የሆነችው ሕንድ ያላትን ዘላቂ የዲሞክራሲ ጥንካሬ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሕንዱን አቻቸውን የታመኑ ወዳጅ እና ታላቅ ወንድሜ ሲሉ የገለጿቸው ሲሆን፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነትም በታሪክ፣በአጋርነት እና ለሕዝቦቻቸው ባላቸው የጋራ ምኞት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ትስስር መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ እና ሕንድ ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር እና የጀመሩትን የጋራ ጉዞ አብሮ ለመቀጠል ኢትዮጵያ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የኳታር ኤሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል-ታኒ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ
Jun 24, 2026 447
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-የኳታር ኤሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል-ታኒ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የኳታሩ ኤሚር የብልጽግና ፓርቲ በጠቅላላ ምርጫው ያስመዘገበውን ድል ተከትሎ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንኳን ደስ አላችሁ የደስታ መግለጫ መልዕክት ልከዋል። ኤሚሩ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ስኬትን የተመኙ ሲሆን፣በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ እንዲያድግና እንዲጠናከር ያላቸውን ፅኑ ፍላጎትም ገልጸዋል።
የብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ
Jun 24, 2026 432
አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-የብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የብሩንዲ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ኤቫሪሲቴ ንዳይሺሚዬ በህብረቱ እና በብሩንዲ ስም፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ለብልጽግና ፓርቲ ላስመዘገቡት ድል እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እወዳለሁ ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ይህ በምርጫ የተገኘው አዲስ የዲሞክራሲያዊ ውክልና ማረጋገጫ፣የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀገሪቱን ወደ ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋት እና የኢኮኖሚ ዕድገት ለመምራት በጠቅላይ ሚኒስትሩ አመራር ላይ ያለውን ጥልቅ እምነትና መተማመን በተግባር ያሳየበት መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ታሪካዊት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ጠንካራ፣ የተባበረች እና የበለጸገች ሆና መቀጠሏ ለአህጉራዊው የጋራ አጀንዳችን ስኬት ምንጊዜም ቢሆን ወሳኝ መሠረት ነው ብለዋል። ፕሬዝዳንት ኤቫሪስቴ በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ብሩንዲ ከኢትዮጵያ ጋር ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከርና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት ገልጸው፥ ለአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔ የሚለውን መርህ በጋራ ለማሳካት የጀመሩትን የቅርብ ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ይበልጥ የተባበረች፣የበለጸገች እና ሰላማዊ አፍሪካን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ፣ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነትና አጋርነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመልክተዋል።
ፖለቲካ
ለዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች
Jun 24, 2026 50
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሚጀመረው ዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። ለዋናው ሀገራዊ ምክክሩ የሚቀርቡ ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች 1- የሀገር ግንባታ 2 -የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት 3 -የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬደዋ 4- የሃይማኖት ጉዳዮች 5- የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች 6 -ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች 7 -ሙስናና መልካም አስተዳደር 8 -ሰላም ግንባታ
ለዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስምንት አጀንዳዎች ተለይተዋል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Jun 24, 2026 147
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ለዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ስምንት አጀንዳዎች መለየታቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ እንደሚካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል። በዛሬው እለትም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን ይፋ አድርጓል። በመርሀ ግብር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያን ጨምሮ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፥ ኮሚሽኑ ሁሉን አቀፍ ሂደትን በመከተል የተዋጣ ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል። በዚህም ስምንት ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው አጀንዳዎች ተለይተው ለዋናው የምክክር ጉባኤ መለየታቸውን ጠቁመዋል። ይፋ የተደረጉት ስምንቱ አጀንዳዎች የተቀረጹት ራሰን በቻለ ግልጽ ሥርዓተ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽኑ ላለፉት አራት ዓመታት ሰፊ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል፤ በተለያዩ ምዕራፎች ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የሚያስችል አሳታፊና አካታች የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሥራ ተሰርቷል። በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶችን በሰለጠነ ምክክር ለመፍታትና ሀገራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል ምኅዳር ተፈጥሯል። በኢትዮጵያ በሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮችና በውጭ ዓለማት ከሚኖሩ ዜጎች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር መድረክ ተካሂዷል። የሀገራዊ ምክክሩ የእስካሁን ሂደትም ግልጽ፣ ገለልተኛ፣ አካታችና አሳታፊነቱን ጠብቆ የተካሄደ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሕዝባዊ ውይይቶች አጀንዳዎችን ያሰባሰበበት የእስካሁኑ የምክክር ሂደት ቁልፍ ባሕርያት
Jun 24, 2026 192
ባለድርሻ አካላት እንደሀገር ያልተግባባንባቸውን እጅግ መሠረታዊ የሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች በውይይት በማዳበር ለኮሚሽኑ ማስረከባቸው፤ የብዙ ባለድርሻ አካላት ሕመሞች፣ ሥጋቶች፣ ምኞቶች እና ተስፋዎች በአጀንዳ መልክ መቅረባቸው፤ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለምክክሩ ሂደት የሚጠቅሙ እጅግ በርካታ ግብዓቶችን መሰብሰቡ፤ በአንፃራዊነት የተሳታፊዎችን ምቾት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለተሳታፊዎች ቅርብ ናቸው ተብለው በሚታሰቡ ቦታዎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት መከናወኑ፤ በሕዝባዊ ውይይት አጀንዳን የመሰብሰብ ሥራ ሁለት ዓመታትን ፈጅቷል፤ በአጠቃላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔው መካሄድ እንደ ቅድመ ሁኔታ በማገልገል የራሱን ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ምክክር
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡን ወሳኝነት በግልጽ አረጋግጧል - የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Jun 24, 2026 245
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡን ወሳኝነት በግልጽ ያረጋገጠና ለሁሉም አካላት ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ ነው ሲል የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ። ምክር ቤቱ ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን የሕዝብ ድምጽ አግኝቶ ማሸነፉን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላልፏል። በመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክቱም፤ የክልላችንንና የሀገራችንን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ለመቅረፍ በትብብር፣ በፉክክርና በአንድነት መርኅ ላይ በመንተራስ ከመንግሥት እና ከገዥው ብልጽግና ፓርቲ ስሠራ ቆይቻለሁ ብሏል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫም በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩሉን መሥራቱን ጠቁሞ፤ የፓርቲዎቻችንን ፕሮግራም በተለያዩ አመራጮች ለሕዝብ በማቅረብ ለመወዳደር የቻልንበት ጊዜ ነበር ነው ያለው፡፡ አጠቃላይ የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን የሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ርብርብ ከፍተኛ እንደነበር አውስቶ፤ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላትም ውጤቱን ተቀብለው ለሕዝቡ ውሳኔም ተገዥ መሆናቸውን ለኢዜአ በላከው መረጃ አረጋግጧል። በዚህም መሠረት፤ ምርጫው በሰላም ተጠናቆ ሀገራችን ስላሸነፈች ለመላው ሕዝባችን እንኳን ደስ አላቸሁ ለማለት እንወዳለን ብሏል የጋራ ምክር ቤቱ። የምርጫው ሂደትና ውጤቱም ዴሞከራሲያዊና የሕዝብን ወሳኝነት ያረጋገጠ በመሆኑ የሕዝቡን ድምጽ በጸጋ እንቀበላለን ሲልም አስታውቋል። በዚህ ታሪካዊ የምርጫ ሂደት ውስጥ ለተሳተፉት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ለሁሉም ባለድርሻ አካላትም ምክር ቤቱ ምሥጋና አቅርቧል። በመጨረሻም ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን የሕዝብ ድምጽ አግኝቶ ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባረጋገጠው መሠረት፤ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለብልጽግና ፓርቲ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን በቀጣይ ክልላዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ ነን ሲል አረጋግጧል። በአጠቃላይ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝቡን ወሳኝነት በግልጽ ያረጋገጠና ለሁሉም አካላት ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ መሆኑንም ነው ያስታወቀው። በተጨማሪም ለሀገራችን የዴሞከራሲ ምኅዳር መስፋት ዐሻራ ጥሎ ያለፈ በመሆኑ፤ ሁሉም አካላት ይህንን ጅምር ሂደት ወደ ከፍተኛ ደረጃ ለማድረስ መሥራትና ከምርጫ ማግስት ጀምሮ ፊታችንን ወደ ልማትና ሰላም ግንባታ በማዞር በሁሉም ዘርፍ ለውጥ ለማምጣት መትጋት ይኖርብናል ነው ያለው፡፡ ብልጽግና ፓርቲም ሕዝቡ የሰጠውን አደራ በጥንቃቄ በመያዝ የሕዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ ሌት ተቀን ተግቶ እንዲሠራ ጠይቋል።
ሰላማዊና የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት ኢትዮጵያና ብሩንዲ በጋራ ይቆማሉ-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jun 24, 2026 611
አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያና ብሩንዲ ሰላማዊና የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት ባላቸው የጋራ ቁርጠኝነት ዙሪያ አብረው እንደሚቆሙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ በሀገራቸው እና በአፍሪካ ህብረት ስም ያስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ትልቅ ብርታትን የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ብሩንዲ በጥልቅ የወንድማማችነት ትስስር፣እንዲሁም ሰላማዊና የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት ባላቸው የጋራ ቁርጠኝነት ዙሪያ አብረው ይቆማሉ ብለዋል። ለሁለቱ ሀገራት ወዳጅነት ትልቅ ዋጋ እንደሚሰጡ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሕዝቦቻችንና የአፍሪካን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጠውን ይህንን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ኢትዮጵያ ዝግጁ መሆኗን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ ከህንድ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ትሻለች-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jun 24, 2026 493
አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያ ከህንድ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማሳደግ እንደምትፈልግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሞዲ ያገኙትን ታሪካዊ የሕዝብ ውክልና የአለማችን ትልቁ ዲሞክራሲ የሆነችው ሕንድ ያላትን ዘላቂ የዲሞክራሲ ጥንካሬ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሕንዱን አቻቸውን የታመኑ ወዳጅ እና ታላቅ ወንድሜ ሲሉ የገለጿቸው ሲሆን፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነትም በታሪክ፣በአጋርነት እና ለሕዝቦቻቸው ባላቸው የጋራ ምኞት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ትስስር መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ እና ሕንድ ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር እና የጀመሩትን የጋራ ጉዞ አብሮ ለመቀጠል ኢትዮጵያ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የኳታር ኤሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል-ታኒ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ
Jun 24, 2026 447
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-የኳታር ኤሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል-ታኒ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የኳታሩ ኤሚር የብልጽግና ፓርቲ በጠቅላላ ምርጫው ያስመዘገበውን ድል ተከትሎ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንኳን ደስ አላችሁ የደስታ መግለጫ መልዕክት ልከዋል። ኤሚሩ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ስኬትን የተመኙ ሲሆን፣በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ እንዲያድግና እንዲጠናከር ያላቸውን ፅኑ ፍላጎትም ገልጸዋል።
የብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ
Jun 24, 2026 432
አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-የብሩንዲው ፕሬዝዳንት ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የብሩንዲ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ኤቫሪሲቴ ንዳይሺሚዬ በህብረቱ እና በብሩንዲ ስም፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ለብልጽግና ፓርቲ ላስመዘገቡት ድል እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እወዳለሁ ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ይህ በምርጫ የተገኘው አዲስ የዲሞክራሲያዊ ውክልና ማረጋገጫ፣የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀገሪቱን ወደ ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋት እና የኢኮኖሚ ዕድገት ለመምራት በጠቅላይ ሚኒስትሩ አመራር ላይ ያለውን ጥልቅ እምነትና መተማመን በተግባር ያሳየበት መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ታሪካዊት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ጠንካራ፣ የተባበረች እና የበለጸገች ሆና መቀጠሏ ለአህጉራዊው የጋራ አጀንዳችን ስኬት ምንጊዜም ቢሆን ወሳኝ መሠረት ነው ብለዋል። ፕሬዝዳንት ኤቫሪስቴ በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ብሩንዲ ከኢትዮጵያ ጋር ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከርና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት ገልጸው፥ ለአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔ የሚለውን መርህ በጋራ ለማሳካት የጀመሩትን የቅርብ ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ይበልጥ የተባበረች፣የበለጸገች እና ሰላማዊ አፍሪካን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ፣ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነትና አጋርነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመልክተዋል።
ማህበራዊ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ለመምህራን ልማት ትኩረት ተሰጥቷል
Jun 24, 2026 69
አርባ ምንጭ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚከናወኑ ተግባራት ለመምህራን ልማት ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው "በቅቶ ማብቃት ልቆ ማላቅ" በሚል መሪ ሃሳብ ለቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራን የአሠልጣኞች ስልጠና በአርባምንጭ ከተማ እየሰጠ ነው። የቢሮ ሃላፊው አብዮት ደምሴ ስልጠናው ዛሬ ሲጀመር እንደገለጹት በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሰው ሀይል ልማትና ግብአት አቅርቦት ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። ለዚህም ሀገር አቀፍ የትምህርት ፍኖተ ካርታውን በመተግበር የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ላይ ይበልጥ ለመስራት የመምህራን አቅም ማጎልበት ላይ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል። ዛሬ የተጀመረው የመምህራን የአሠልጣኞች ስልጠናም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑን ጠቁመዋል። ስልጠናው የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራንን አቅም በማጎልበት ህጻናትን በአሳታፊ ዘዴ እና በተግባራዊ እንቅስቃሴዎች የማስተማር ክህሎትን ለማዳበር አጋዥ መሆኑን አስታውቀዋል ። የቢሮው ምክትልና የመምህራን ትምህርት አመራር ልማት ዘርፍ ሃላፊ ታምራት ይገዙ (ዶ/ር) በበኩላቸው ትምህርት ለሀገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት መሰረት በመሆኑ ዘርፉን በእውቀት መምራት ይገባል ብለዋል ። ለዚህም የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራን የሙያ ብቃት ማጎልበቻ እና የደረጃ ማሟያ ስልጠና በየጊዜው ከመስጠትም በላይ መምህራን የትምህርት ደረጃቸውን እንዲያሻሽሉ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። ስልጠናው በቅቶ የሚያበቃና ልቆ የሚያልቅ መምህራንን በማፍራት ብቁ ትውልድ ለመገንባት ወሳኝ ነው ያሉት ደግሞ የአርባምንጭ ትምህርት ኮሌጅ ዲን እንግዳ እንድሪያስ (ዶ/ር) ናቸው። የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የህፃናትን የመማር ፍላጎት፣ ክህሎትና ስብዕና መሠረት አድርጎ መስራት አስገዳጅ መሆኑን አስረድተዋል ። ለዚህም ለአመቻች መምህራን የሙያ ብቃትን ማሳደግና ግብአትን ማሟላትን ይጠይቃል ብለዋል። የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ሀገርና ትውልድ ለመገንባት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ መጠናከር እንደሚገባውም አክለዋል።
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 513
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልየነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
በምዕራብ ወለጋ ዞን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማህበራዊ ችግሮችን እየፈታ ነው
Jun 24, 2026 296
ጊምቢ፡ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ወለጋ ዞን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መረዳዳትን በማጠናከር ማህበራዊ ችግሮችን እየፈታ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። በምዕራብ ወለጋ ዞን የዘንድሮ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በቆንዳ ወረዳ የአቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት በማደስ ተጀምሯል። የዞኑ አስተዳደሪ አቶ ተሊላ ተረፈ በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፤ በዞኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህዝቡን የመረዳዳት ባህልና እሴት በማጠናከር ማህበራዊ ችግሮችን እየፈታ ነው። ወጣቶች ጊዜና ጉልበታቸውን በበጎ ፈቃድ ስራ ላይ ለማዋል ያሳዩት ተነሳሽነት የዞኑ ልማት ለማፋጠን እያገዘ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ይህንን በጎ ተግባር በተጠናከረ መልኩ በማስቀጠል ለተቸገሩ ወገኖቻችን ልንደርስላቸው ይገባል ሲሉም አመልክተዋል። የምእራብ ወለጋ ዞን ሴቶችና ህጻናት ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አልማዝ መኮንን በበኩላቸው በዞኑ ከ1 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር ላይ እንደሚሳተፉ ገልጸዋል። በአገልግሎቱም ከ800 ሺህ በላይ የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል። በዞኑ ከዚህ ቀደም በክረምት እና በበጋ ወራት ወጣቶችን በማስተባበር እየተሰራ ያለው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ውጤታማ እንደነበር ጠቁመው፤ በዚህም የበርካታ ወገኖች ችግር እየተቃለለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የሴቶች ማብቃትና የሥርዓተ-ፆታ እኩልነት ፖሊሲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ አለው
Jun 24, 2026 401
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ አዲሱ ብሔራዊ የሴቶች ማብቃትና የሥርዓተ-ፆታ እኩልነት ፖሊሲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ከማጠናከር አንጻር ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ከይረዲን ገለፁ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 55ኛ መደበኛ ስብሰባ ብሔራዊ የሴቶች ማብቃትና የሥርዓተ ፆታ እኩልነት ረቂቅ ፖሊሲ ማፅደቁ ይታወሳል። የፀደቀው ፖሊሲም ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን ለመከላከል እና ጥበቃና ምላሽ ለመስጠት፣ ልዩ ትኩረት ለሚሹ ሴት አካል ጉዳተኞች እና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ ለሆኑ ሴቶች ምላሽ ለመስጠት ፋይዳው የጎላ መሆኑ መገለፁ ይታወቃል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ብሔራዊ የሴቶች ማብቃት እና የስርዓተ ፆታ እኩልነት ፖሊሲን ወደ ተግባር ለማስገባት በፌዴራል ባሉ ተቋማቶች እንዲሁም በክልሎች ለሚገኙ የስራ ሃላፊዎች ለሶስት ቀናት የሚቆይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በየደረጃው ላሉ አመራሮች መስጠት ጀምሯል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ከይረዲን ስልጠናውን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለፁት፤ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው ፖሊሲ ነባራዊ ሁኔታን ታሳቢ አድርጎ የተዘጋጀ ባለመሆኑ አሁን ላይ ዘመኑን በሚዋጅ መልኩ እንዲሻሻል መደረጉን አስረድተዋል። አሁን የተሻሻለው ብሔራዊ የሴቶች ማብቃት እና የሥርዓተ-ፆታ እኩልነት ፖሊሲ እነዚህን ችግሮች በመፍታት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን በሚመጥን መልኩ ሴቶችን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል። ፖሊሲው ስር ነቀል የሆኑ ጉዳዮች ላይ በቂ ትኩረት የሚሰጥ እንዲሁም ጥበቃና ምላሽ ለመስጠት እንደሚረዳም ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ስርዓተ-ጾታን መሰረት ካደረጉ አለም አቀፍና አህጉራዊ ስምምነቶች ጋር የተጣጣመ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
ኢኮኖሚ
ረቂቅ አዋጁ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት የሚደግፍ ነው
Jun 24, 2026 246
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት የሚደግፍ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ይፋዊ የሕዝብ መድረክ አካሂዷል፡፡ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን በዚሁ ወቅት፤ በሕዝብ መድረኩ ለተሳተፉ አካላት ስለ ብሔራዊ የካርበን ግብይት ረቂቅ አዋጁ ይዘትና አስፈላጊነት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸው፤ የካርበን ግብይት የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የተዘረጋ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት መሆኑን ጠቅሰው ዓላማውም ወደ ከባቢ አየር የሚለቀቀውን በካይ ጋዝ መጠን ማስወገድ፣ መቀነስ እና መከላከል ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ይህንን ለመተግበር በፖሊሲ የተደገፈ ተግባር እያከናወነች እንደምትገኝም ጠቁመው ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ማስገኘት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ በዛሬው ዕለት ለሕዝብ ውይይት ይፋ የተደረገው ረቂቅ አዋጅ በሀገራችን የካርበን ገበያ ልማት ላይ ወሳኝ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ጠቅሰው የካርቦን ግብይት ኢትዮጵያ ከዘርፉ ተጨማሪ የፋይናንስ ምንጭ የምታገኝበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የበካይ ጋዝ የልቀት መጠን እንዲቀንስ በማድረግ የአረንጓዴ እና የዘላቂ ልማት ግቦች እንዲሳኩ እንደሚያደርግም እንዲሁ፡፡ በሕዝብ መድረኩ የተሳተፉት የአረንጓዴ ዐሻራ ቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ ረቂቅ አዋጁ ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ የሰጠችውን ትኩረት በግልጽ የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ የካርበን ግብይት ለሀገራችን እንደ አንድ ተጨማሪ የኢንቨስትመንት አማራጭ ሆኖ ስለሚያገለግል ሂደቱ በተፋጠነ መልኩ ወደ ተግባር መግባት እንዳለበት አመላክተዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጀ፤ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነቶችን ከፈረሙ ሀገራት አንዷ መሆኗን ገልጸዋል። ይህ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ የተበታተኑ አሠራሮችን ወደ አንድ በማምጣት፣ የካርበን ግብይትን በተሟላ እና ግልጽ በሆነ የሕግ ማዕቀፍ ለመምራት ያስችላል ብለዋል። ረቂቅ አዋጁ ሀገሪቱ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት የሚደግፍና ለተግባራዊነቱ ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑንም ጠቁመዋል። በተጨማሪም አረንጓዴ ልማትን እና የታዳሽ ኃይል አጠቃቀምን የሚያበረታታ በመሆኑ፣ ሀገራችን ከምታመነጨው የካርቦን ልቀት ገቢ እንድታገኝ ያደርጋታል ብለዋል። ይህ ወሳኝ ሰነድ ጸድቆ ወደ ተግባር ሲገባ የኢትዮጵያ የካርበን ግብይት ግልጽ መመሪያና ሥርዓት እንዲኖረው ለማድረግ ከፍተኛ እገዛ ይኖረዋል ብለዋል። በመሆኑም አዋጁ አስፈላጊዎቹን የዝግጅት ሒደቶች በሙሉ አልፎ ለትግበራ እንዲበቃ ቋሚ ኮሚቴው የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አረጋግጠዋል።
በዞኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው
Jun 24, 2026 250
ጊምቢ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ወለጋ ዞን የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆናቸውን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ። በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ወረዳ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ መሰረተ ልማት ግንባታዎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። በወቅቱም የኦሮሚያ ክልል የመንገድ እና ሎጂስቲክስ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታዬ ጉዲሳ በክልሉ ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ ናቸው። መሰረተ ልማቱም በአጭር እና በረጅም ጊዜ እቅድ የተገነቡ መሆኑንና በህዝቡና በአጋር አካላት ተሳትፎ መከናወናቸውን ጠቅሰው ተግባራቱም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የክልሉ መንግስት የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ባለው ቁርጠኝነት በርካታ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት ኃላፊው ዛሬ በዞኑ የተመረቁት ፕሮጀክቶችም የዚሁ ማሳያ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምዕራብ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፈ በበኩላቸው በዞኑ ለነዋሪዎች የመሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ግንባታዎች በጥራትና በተያዘላቸው ጊዜ ተገንብተው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተሰራ ነው ብለዋል። የዚሁ አካል የሆኑትና በበጀት ዓመቱ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ተናግረዋል። በቀጣይም በዞኑ የህዝቡን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
በተደመረ አቅም የግብርና ምርታማነትን በማስፋትና በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት በልዩ ትኩረት እየተሰራበት ነው- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Jun 24, 2026 309
ዱራሜ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በተደመረ አቅም የግብርና ምርታማነትን በማስፋትና በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት በልዩ ትኩረት እየተሰራበት መሆኑን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። "የተቀናጀ የግብርና ትጋት ለላቀ ምርታማነት" በሚል መሪ ሀሳብ የመኸር ወቅት የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራዎች የንቅናቄ መድረክ በዱራሜ ከተማ ተካሄዷል። ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ ከተረጂነት ለመውጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚያግዙ የግብርናው ዘርፍ የልማት ስራዎች ይጠናከራሉ። በክልሉ በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ ስለመምጣቱም አስረድተዋል። የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራም የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ይገኛል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ተግባሩን ማላቅ እንደሚገባም ጠቁመዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በበኩላቸው በክልሉ በ2018/19 የመኸር ወቅት 800 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ ማሳ ይለማል ብለዋል። በዚህም 70 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ለማምረት ግብ ተቀምጦ ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመዋል። ክልሉ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ እያከናወናቸው በሚገኙ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በተለይም የአካባቢን ፀጋ ለይቶ በማልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው እሳቤ እውን በማድረግ የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ ስለመምጣቱም ጠቁመዋል። በዚህም አርሶ አደሩ ከቤት ፍጆታው አልፎ ለገበያና ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን ማምረት ስለመጀመሩና ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል። የንቅናቄ መድረኩ በመኸር ወቅት የታቀደውን ግብ ለማሳካት የጋራ ተግባቦት ለመፍጠር እንደሚያግዝና አመራሩና የግብርና ባለሙያው ለእቅዱ መሳካት የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ በበኩላቸው በዞኑ የመኸር ወቅት የግብርና ልማት 47 ሺህ ሄክታር ማሳ ስንዴንና ገብስን ጨምሮ በሌሎች ዋና ዋና ሰብሎች ይለማል ብለዋል። በዞኑ የኩታ ገጠም እርሻ ትግበራ ለምርታማነት ማደግ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ጠቅሰው በመኸር ወቅት የግብርና ልማትም ስነ-ዘዴው በትኩረት ተግባራዊ እንደሚደረግም ገልጸዋል።
በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
Jun 24, 2026 212
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚዛን አማን ከተማ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። የሚዛን አማን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የ5 ኪሎሜትር ኮሪደር ልማትና የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ መናኸሪያ ዛሬ ተመርቀዋል ። ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ልማቶችን ማስፋፋትና ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው። በዚህ እንቅስቃሴ ውሰጥ የሕዝቡ ተሳትፎ እያደገ በመምጣቱ ትላልቅ መሠረተ ልማቶችን በመገንባት ለአገልግሎት ማዋል እየተቻለ መሆኑን ገልጸዋል። ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው የሚዛን አማን መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በቴክኖሎጂ ታግዞ ተቋማትን በማስተሳሰር ተገልጋዮችን ከብልሹ አሠራር የሚታደግ ነው ብለዋል። መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰው በሌሎች የክልሉ ከተሞችም ተደራሽ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል። በተመሳሳይ ዛሬ ወደ አገልግሎት የገባው የሚዛን አማን መናኸሪያ የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያሳልጥ መሆኑን ጠቁመዋል። የኮሪደር ልማት ስራም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስታውቀዋል። የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በዞኑ በመንግስትና በህዝብ ተሳትፎ የተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለዚህም ለምረቃ የበቃውን የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን ለአብነት ጠቅሰዋል ። የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ሌዊ በከተማው የተመረቁ ፕሮጀክቶች ለሕዝብ ጥያቄ ምላሽ የሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል ። የልማት ፕሮጀክቶቹ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከተማውን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ምቹ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል ። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ያሲን የካ እና ወይዘሮ ጥሩዬ ከበደ በከተማው በሚከናወኑ የልማት ስራዎች ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል ።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በኦሮሚያ ክልል ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አባወራዎች በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የሶላር ፓኔል ተሰራጭቷል
Jun 24, 2026 241
አዳማ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አባወራዎች በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የሶላር ፓኔል ስርጭት መከናወኑን የክልሉ ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ገለጸ። በቢሮው የኢነርጂ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሶሬሳ እንደገለጹት፤ በክልሉ በቤተሰብ ደረጃ የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ላይ በትኩረት እየተሠራ ነው። በዚህም ከዋናው የኃይል ቋት ርቀው የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የሶላር ፓኔል ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አባወራዎች መሰራጨታቸውን ገልጸዋል። የታዳሽ ኃይል ልማትና ተደራሽነት የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። በሌላ በኩል ከዋናው የኃይል ቋት ርቀው የሚገኙ የገጠር የጤናና የትምህርት ተቋማት የኃይል አቅርቦት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም በናፍጣ የሚሠሩ የውኃ ተቋማትን ወደ ፀሐይ ኃይል በመቀየር ኅብረተሰቡ ዘላቂ የመጠጥ ውኃ አገልግሎት እንዲያገኝ መሠራቱንም ጠቁመዋል። በተያያዘም ከ700 ሺህ በላይ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችንና ከ1 ሺህ 500 በላይ የባዮ ጋዝ በመሥራት ለመብራት አገልግሎት እንዲሁም ተረፈ ምርቱ ለተፈጥሮ ማዳበሪያ እንዲውል መደረጉን ጠቁመዋል፡፡
በቀጣዩ ዓመት በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለመስጠት ግብ ተይዟል
Jun 24, 2026 362
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በቀጣዩ ዓመት በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል አንድ ማዕከል አገልግሎት ለመስጠት ግብ መያዙን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት ከመቀነስ ባሻገር የመልካም አስተዳደር ችግሮች ትርጉም ባለው መልኩ እንዲቀነሱ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአቃቂ ቃሊቲ 10ኛውን፤ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ደግሞ 11ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን መርቀው ስራ አስጀምረዋል። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ፤የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድርን ጨምሮ የመዲናዋ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር የመንግሥት አገልግሎት ቢሮክራሲ፣ ውጣ ውረድ እና እንግልት የበዛበት እንደነበር አስታውሰዋል። የመልካም አስተዳደር ችግር ዜጎች አገልግሎት በአግባቡ እንዳያገኙ ተግዳሮት ሆኖ መቆየቱን አመልክተው፤ የመሶብ አንድ ማዕከል የዲጂታል አገልግሎት ለችግሮች ሁነኛ መፍትሔ መሆኑን ገልጸዋል። በቁርጠኝነት ከሰራን የማይለወጥ ነገር እንደሌለ በአንድ ማዕከል አገልግሎት ያመጣነው ውጤት ትልቅ ማሳያ ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፥ ብልሹ አሰራር ከመሠረቱ እየተቀረፈ ነው ብለዋል። የአገልግሎት ተደራሽነትን ይበልጥ ለማስፋት ዜጎች በተንቀሳቃሽ ስልካቸው አገልግሎት የሚያገኙበት ሂደት እንደሚጠናከርም ተናግረዋል። በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመንግሥት ከሚሰጡ አገልግሎቶች 50 የሚሆኑት ወደ አንድ ማዕከል እንዲገቡ መደረጉን ጠቅሰው፥ በቀጣዩ ዓመት ሙሉ ለሙሉ ለማስገባት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። አገልግሎት አሰጣጥ ላይ አሁንም ቀሪ ስራዎች አሉ ያሉት ከንቲባ አዳነች፥ የዜጎችን እርካታ የሚያሳድጉ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ለሕዝብ የገባነውን ቃል ወደ ተግባር እየቀየርን ብልጽግናችንን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል።
ኢትዮጵያ አስተማማኝ እና ሁሉን አቀፍ የዲጂታል መጻኢ ዕድልን ለመገንባት በቁርጠኝነት እየሠራች ነው
Jun 24, 2026 286
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አስተማማኝ እና ሁሉን አቀፍ የዲጂታል መጻኢ ዕድልን ለመገንባት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ገለጹ። በሳይበር ደህንነት እና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ላይ ያተኮረና ለሁለት ቀናት የሚቆይ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ እየተመራች በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞዋ ላይ አዲስና ተስፋ ሰጪ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ቴክኖሎጂ ለሀገራዊ ልማት መሠረታዊ አጋዥ ተደርጎ እየተወሰደ እንደሚገኝም አብራርተው፤ ደህንነቱ የተጠበቀ የዲጂታል ሥነ-ምህዳር የቴክኖሎጂ አስፈላጊነት ብቻ ሳይሆን የሀገር ሉዓላዊነት፣ የኢኮኖሚ ጥንካሬ እና የዘላቂ ልማት መሠረታዊ ምሰሶ መሆኑንም ገልጸዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች የግብርና ዘመናዊነትን እያፋጠኑ፣ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ አቅምን እያሰፉ፣ የሀገር ውስጥ የፈጠራ ሥነ-ምህዳርንና የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዞችን ከመደገፍ ባሻገር ወሳኝ የዲጂታል ሥርዓቶችን በራስ የማልማት ብሔራዊ አቅምን እያጠናከሩ መሆኑን ጠቁመዋል። የአህጉሪቱን የዲጂታል መጻኢ ጉዞ ለማረጋገጥም በሳይበር ደህንነት፣ በትምህርት፣ በላቀ ቴክኒክ ሥልጠና፣ በምርምርና ፈጠራ እንዲሁም በወጣቶች ተሰጥኦ ማልማት ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እየተደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ትብብርን ለማሳደግ፣ ኃላፊነት የተሞላበት ፈጠራን ለማበረታታት፣ የአቅም ግንባታን ለማጠናከር እና የመረጃ ልውውጥን ለማመቻቸት ከመንግሥታት፣ ከአለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ከአካዳሚክ ማኅበረሰብ እና ከኢንዱስትሪ መሪዎች ጋር በቅንጅት እየሠራች መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ማኅበር ፕሬዚዳንት ብርሃኔ በየነ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኮንፈረንሱ የአፍሪካን የሳይበር ደህንነት አቅምና የዳታ ሉዓላዊነትን ለማጠናከር እንዲሁም የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አጠቃቀምን ለማበረታታት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካን የሳይበር ደህንነት አቅምን ማሳደግ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በዘርፉ ያሉ የክህሎትና የአቅም ክፍተቶችን መለየት የጉባኤው ዋነኛ ትኩረት መሆኑን ተናግረዋል። በአፍሪካ ቀጣናዊ ትብብርን በመገንባት ደህንነቱ የተጠበቀ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ ይህ መድረክ ለእውቀት ሽግግርና ለተግባራዊ የመፍትሄ ሐሳቦች መፈጠር ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) የፕሮግራም ድጋፍ ምክትል ዋና ጸሐፊ ማማ ኬይታ በበኩላቸው፤ አፍሪካ ያሏትን ምቹ ሁኔታዎች ወደ ዘላቂ የዲጂታል መፍትሄዎች የመቀየር ታሪካዊ ዕድል እንዳላት ገልጸዋል። አህጉሪቱ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ከመሆን ወጥታ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋን በራሷ መቅረጽ የምትችለው የዲጂታል ሽግግርን እና የፈጠራ ሥነ-ምህዳሮችን በቁርጠኝነት ስትደግፍ መሆኑን አስገንዝበዋል። ለዚህም ስኬት ጠንካራ ፖሊሲዎችን መቅረጽ፣ አዳዲስ ተነሳሽነቶችን መጀመር፣ ኢንቨስትመንቶችን ማንቀሳቀስ እና የተጀመሩ የተቀናጀ የጋራ ቁርጠኝነት ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ማንሠራራት ጠንካራ መሠረት እየገነባች ነው
Jun 24, 2026 290
አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ማንሠራራት በመሠረተ ልማት፣ በተቋማዊ አቅምና በዲጂታል ክህሎት ጠንካራ መሠረት እየገነባች እንደምትገኝ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም ሰዒድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ሀሳብ የ“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ጉባኤ ተካሂዷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም ሰዒድ፤ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ተበታትነው የቆዩ አሠራሮችን በዲጂታል ማንነት፣በክፍያ እና በዳታ ልውውጥ የተቀናጁ የኢኮኖሚ መዋቅሮች ውስጥ በማስገባት ለሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምቹ የሆነ ምህዳር እየገነባች መሆኑን አመልክተዋል። የመንግሥት አገልግሎቶችን በማገናኘት እንዲሁም የሀገር በቀል አቅምን በጋራ በማሳደግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ኢኮኖሚያዊ እድገት በምርት፣ በወጪ ንግድ እና በኢንቨስትመንት አቅሞች ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ወደ ተሻለ ዕድገት ለማሸጋገር የዲጂታል አሠራሮች መጠናከር ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የዲጂታል ስትራቴጂዎች ትግበራ በማዕድን፣ በግብርና፣ በከተሞች እና በመሠረተ ልማት ላይ ሰፊ በሆነ የኢኮኖሚ ሽግግር ውስጥ በስፋት እያሳየች መሆኑን ገልጸዋል። የዲጂታል አገልግሎትን የሚያፋጥኑ መሠረተ ልማቶች ላይ ትኩረት አድርጎ መሠራቱ የክፍያ ሥርዓቶች በኢኮኖሚው ውስጥ የምዝገባ፣ የግብይት እና ሌሎች እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡ እያደረገ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ይህንኑ የዲጂታል ሪፎርም ወደ ምርታማነት ለመቀየር ለዘርፉ ዕድገት ማነቆ የሆኑትን የፋይናንስ ችግር፣የባለሙያዎች አቅም ውስንነት መፍታት ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል። ሀገሪቱ ቴክኖሎጂ መጠቀም የሚችል ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራትም የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች መሆኗን ተናግረዋል። በአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ በርካታ ዜጎችን የማብቃት ሥራ በስፋት እየተሠራ መሆኑንም አክለዋል። ኢትዮጵያ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማትና ትግበራ የሚሆን ተቋማዊ፣ የሰው ሃይልና የቴክኖሎጂ አቅም ላይ ትኩረት መስጠቷንም አንስተዋል። የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ፣በዓለም አቀፍ ደረጃ ልዩ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን፣ ሥርዓት ፈጣሪዎችን ለማሰልጠን እና ምርምርን ከተግባር ጋር ለማገናኘት የተነደፈ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።
ስፖርት
ሞሮኮ ከሃይቲ፤ ደቡብ አፍሪካ ከኮሪያ ሪፐብሊክ የዓለም ዋንጫ ወሳኝ የምድብ ጨዋታዎች
Jun 24, 2026 319
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):- የ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ። ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ ሞሮኮ ከሃይቲ በአትላንታ ስታዲየም ይጫወታሉ። ከሁለት ጨዋታዎች አራት ነጥብ ያገኘችው ሞሮኮ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። ሞሮኮ ካሸነፈች በቀጥታ ወደ ጥሎ ማለፍ ትገባለች፤ በአቻ ወይም በሽንፈት ውጤት ደግሞ በምርጥ ሶስተኛነት የማለፍ ዕድል ይኖራታል። ከውድድሩ መሰናበቷ የተረጋገጠው ሃይቲ የመጨረሻ ጨዋታዋን ታደርጋለች። በዚሁ ምድብ በተመሳሳይ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ ስኮትላንድ ከብራዚል በሚያሚ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ስኮትላንድ በሶስት ነጥብ ሶስተኛ፣ ብራዚል በአራት ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዘዋል። ማሸነፍ ስኮትላንድን በቀጥታ ወደ ጥሎ ማለፍ ያስገባታል። አቻ መውጣት በሂሳባዊ ስሌት በምርጥ ሶስተኝነት ሊያሳልፋት ይችላል። ብራዚል ካሸነፈች ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቷን ታረጋግጣለች፤ አቻ መውጣት ወይም መሸነፍም ቢሆን ወደ ቀጣዩ ዙር ሊያሳልፋት ይችላል። በተያያዘም የምድብ አንድ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ። በሞንቴሬይ ስታዲየም ደቡብ አፍሪካ ከኮሪያ ሪፐብሊክ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። ደቡብ አፍሪካ በአንድ ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዛለች። ኮሪያ ሪፐብሊክ በሶስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ደቡብ አፍሪካ ወደ ቀጣዩ ዙር ለማለፍ ያላት ብቸኛ እድል የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ ብቻ ነው። በአንጻሩ ኮሪያ ሪፐብሊክ ማሸነፍ ቀጥታ ወደ ጥሎ ማለፍ ያስገባታል። የአቻ ውጤት በምርጥ ሶስተኝነት ሊያሳልፋት የሚችልበት እድል አለ። በዚሁ ምድብ ቼክ ሪፐብሊክ ከሜክሲኮ በተመሳሳይ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በሜክሶኮ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ከአዘጋጆቹ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሜክሲኮ ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቷ ይታወቃል። ካሸነፈች ውይም አቻ ከወጣች የምድቡ መሪ ሆና ታጠናቅቃለች። ቼክ ሪፐብሊክ በአንድ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋዋን ለማለምለም ያላት ብቸኛው እድል ማሸነፍ ብቻ ነው። በምድብ ሁለት ስዊዘርላንድ ከካናዳ በቢሲ ፕሌስ ስታዲየም ምሽት አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ካናዳ እና ስዊዘርላንድ በተመሳሳይ አራት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበላልጠው አንደኛና ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል። አሸናፊው ሀገር በቀጥታ ወደ ጥሎ ማለፍ ይገባል። የአቻ ውጤት ሁለቱንም ብሔራዊ ቡድኖች ወደ ቀጣዩ ዙር ያሳልፋል። ሽንፈት የሚያስተናግደው ቡድን ምርጥ ሶስተኛ ሆኖ የማለፍ እድል አለው። በዚሁ ምድብ ቦሲኒያ እና ሄርዞጎቪና ከኳታር ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ በሲያትል ስታዲየም ይጫወታሉ። ቦሲኒያና ሄርዞጎቪናና ኳታር በተመሳሳይ አንድ ነጥብ በግብ ልዩነት ተበላልጠው ሶስተኛና አራተኛ ደረጃን ይዘዋል። የሀገራቱ ብቸኛ የማለፍ እድል ማሸነፍ ላይ ብቻ የተመሰረተ ነው።
ኮሎምቢያ ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለች
Jun 24, 2026 374
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ 11 ጨዋታ ኮሎምቢያ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ማለዳ ላይ በተጠናቀቀው እና በጓድላሃራ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ዳንኤል ሙኞዝ በ76ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ኮሎምቢያ በተጋጣሚዋ ላይ ፍጹም የጨዋታ ብልጫ ወስዳለች። ውጤቱን ተከትሎ ኮሎምቢያ በስድስት ነጥብ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅላለች። አንድ ነጥብ ያላት ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሶስተኛ ደረጃን ይዛለች። በዚሁ ምድብ ትናንት ማምሻውን በተካሄደው ጨዋታ ፖርቹጋል ኡዝቤኪስታንን 5 ለ 0 አሸንፋለች። ፖርቹጋል በአራት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ስትይዝ ኡዝቤኪስታን ያለ ምንም ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከኡዝቤኪስታን፣ ኮሎምቢያ ከፖርቹጋል የምድብ 11 የመጨረሻ ጨዋታዎች ናቸው። ኮንጎ ወደ ጥሎ ማለፍ ለመግባት ኡዝቤኪስታንን ማሸነፍ ይጠበቅባታል።
ጋና ከእንግሊዝ ጋር አቻ ተለያየች
Jun 24, 2026 327
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ 12 መርሐ ግብር እንግሊዝ እና ጋና ያደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። ማምሻውን በቦስተን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ እንግሊዝ የኳስ ቁጥጥር እና የግብ እድሎችን የመፍጠር ብልጫ ወደ ጎል መቀየር አልቻለችም። የተደራጀ የመከላከል ስልት ይዛ የገባችው ጋና ወሳኝ ነጥብ አግኝታለች። ውጤቱን ተከትሎ እንግሊዝ እና ጋና በተመሳሳይ አራት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበላልጠው አንደኛና ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል። ጋና ወደ ጥሎ ማለፍ የመግባት እድሏን አለምልማለች። በዚሁ ምድብ ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ ፓናማ ከክሮሺያ በቶሮንቶ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሁለቱም ሀገራት በመጀመሪያ ጨዋታቸው ሽንፈት አስተናግደዋል።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ አዲስ የዓለም ዋንጫ ክብረ ወሰን ባስመዘገበበት ጨዋታ ፖርቹጋል በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈች
Jun 23, 2026 803
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የምድብ 11 መርሐ ግብር ፖርቹጋል ኡዝቤኪስታንን 5 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በሂውስተን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ኑኖ ሜንዴዝ፣ ራፋኤል ሊያዎ እና የኡዝቤኪስታኑ ግብ ጠባቂ አብዱቮሂድ ኔማቶቭ በራሱ ላይ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። የ41 ዓመቱ የፖርቹጋል አምበል ክርስቲያኖ ሮናልዶ በስድስት የዓለም ዋንጫዎች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። በዓለም ዋንጫው ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 10 በማድረስ ለፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ብዙ የአለም ዋንጫ ጎል ያስቆጠረው ተጫዋች ሆኗል። ከዚህ ቀደም ኡሴቢዮ ለፖርቹጋል ዘጠኝ ግቦችን በማስቆጠር ክብረ ወሰኑን ይዞ ነበር። ሮናልዶ ከካሜሮኑ ሮጀር ሚላ (42 ዓመት) በመቀጠል በዓለም ዋንጫው ግብ ያስቆጠረ ሁለተኛው አንጋፋ ተጫዋች ሆኗል። በተጨማሪም ሮናልዶ ለሀገሩ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 145 ያደረሰ ሲሆን በእግር ኳስ ህይወቱ ከመረብ ላይ ያሳረፋቸውን ግቦች ብዛት 975 አድርሷል። በጨዋታው የፖርቹጋል የበላይነት በጉልህ ታይቷል። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ድሏን ያስመዘገበችው ፖርቹጋል በአራት ነጥብ የምድብ 11 መሪ ሆናለች። ወደ ጥሎ ማለፍ የመግባት እድሏንም አስፍታለች። በውድድሩ ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ኡዝቤኪስታን ወደ ጥሎ ማለፍ የመግባት እድሏ ጠባብ ሆኗል። ኡዝቤኪስታን ለዓለም ዋንጫው ስትሳተፍ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። በዚሁ ምድብ ኮሎምቢያ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከሌሊቱ 11 ሰዓት ላይ በጓድላሃራ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኮሎምቢያ ያሸነፈች ሲሆን ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ደግሞ አቻ ተለያይታለች።
አካባቢ ጥበቃ
በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርትና ምርታማነት እንዲያድግ አስተዋፅኦ አበርክቷል
Jun 24, 2026 277
ዱራሜ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርትና ምርታማነት እንዲያድግ አስተዋፅኦ ማበርከቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ። ርዕሰ መስተዳድሩ ክልላዊ የክረምት ወራት አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በዱራሜ ከተማ አስጀምረዋል። ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ትግበራ ምርትና ምርታማነት እንዲያድግ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ተግባሩም የአፈር ለምነትን በማስጠበቅና በአየር ንብረት ለውጥ የሚከሰቱ ችግሮችን በመከላከል የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ተጨባጭ ውጤት እንዲመዘገብ ማድረጉን አስረድተዋል። የማህበረሰቡ ችግኝን የመትከል ብቻ ሳይሆን የመንከባከብ ባህል እያደገ ስለመምጣቱም ጠቁመዋል። በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠልም የዘንድሮው የክረምት ወራት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በይፋ መጀመሩን አብስረዋል። በክልሉ በዘንድሮው የክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ530 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉም ጠቁመዋል። በመርሃ ግብሩ ላይም የክልል ፣ የዞንና የልዩ ወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።
በሐረሪ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን አጠናክሮ ለማስቀጠል በቂ ዝግጅት ተደርጓል
Jun 24, 2026 199
ሐረር ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል የሚያስችል በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ አስታወቀ። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ካስገኛቸው ጠቀሜታዎች መካከል የሥራ ዕድል አንዱ ሲሆን በዚህ ረገድ የተሰማሩ ዜጎችም ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ታስቦ በሀገር አቀፍ ደረጃ በስፋት እየተተገበረ የሚገኝ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው። ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በየክረምቱ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ረገድ ከፍተኛ ውጤት እየተመዘገበበት ይገኛል። የሐረሪ ክልል ምንም እንኳን በቆዳ ስፋቱ አነስተኛ እና የከተማ ግብርና የሚበዛበት ክልል ቢሆንም፣ ባለፉት ዓመታት የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄን ከተማን ከማስዋብ፣ የውሃ አማራጮችን ከመጠበቅና የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ከማልማት አኳያ በልዩ ትኩረት ሲተገበር ቆይቷል። በተለይም በክልሉ የሚስተዋለውን የውሃ እጥረት ለመቅረፍ እና የተፋሰስ ልማት ሥራዎችን ለማገዝ በየዓመቱ የሚተከሉ ችግኞች የመጽደቅ ምጣኔን ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ይገኛል። በክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ አራርሶ አደም ለኢዜአ እንዳሉት፤ በክልሉ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል። ለተከላ ከተዘጋጁ ችግኞች ውሰጥ 70 በመቶ የሚሆኑት አትክልትና ፍራፍሬ መሆናቸውንና ቀሪዎቹ ደግሞ ለደንና ለእንሰሳት መኖነት የሚያገለግሉ መሆናቸውን አንስተዋል። አብላጫው ችግኞች በአርሶ አደር ማሳ ውስጥ የሚተከሉ መሆኑን ጠቁመው፤ ቀሪዎቹ የደንና ለእንስሳት መኖነት የሚያገለግሉ ችግኞች ደግሞ በተፋሰሶች፣ እርከኖችና ሌሎች ስፍራዎች ላይ እንደሚተከሉ ገልጸዋል። በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በነገው እለት ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ እንደሚጀመርም ጠቁመዋል። ቀደም ሲል ችግኝ መትከል እንጂ መንከባከብ ላይ ትኩረት አይሰጥም ነበር ያሉት ደግሞ በክልሉ ቂቅሌ ችግኝ ጣቢያ ፎርማን አቶ ምንዳ ጥላሁን ናቸው። አርሶ አደሩ ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚያገኘው ጠቀሜታ በተጨባጭ ውጤት ስላስገኘለትና የችግን ጥያቄዎቹም እያደጉ ስለሚገኝ እኛም የችግኝ ዝግጅት ስራን ከዓመት ዓመት እያሳደግን እንገኛለን ብለዋል። በችግኝ ዝግጅት ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል ወይዘሮ ኢፍቱ አልይ ፤ በችግኝ ዝግጅት ስራ በመሰማራቴ ሀገሬን አረንጓዴ እያለበስኩ ነው፤ በግሌም ተጠቃሚ ሆኛለሁ ብለዋል። በአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ማዘጋጀት ተግባር ተሰማርቼ ተጠቃሚ ሆኛለሁ፤ ልጆቼን አስተምራለሁ ኑሮዬንም እያሻሻልኩበት ነው ያሉት ደግሞ ወይዘሮ መይሙና ያሲን ናቸው።
በዞኑ ከ50 ሺህ ሄክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ የተለያዩ ችግኞች ይተከላሉ
Jun 24, 2026 190
ደብረ ማርቆስ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን በመጪው ክረምት ከ50 ሺህ ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት ላይ የተለያዩ ችግኞች እንደሚተከሉ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የተፈጥሮ ሃብት ቡድን መሪ አቶ ንጉሴ ሽመልስ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩን አጠናከሮ በማስቀጠል ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እየተሰራ ነው። በዚህም በመጪው ክረምት ለሚካሄደው ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚውል ከ264 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በክረምቱ ወቅት ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከ50 ሺህ ሄክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ ችግኞችን ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል። ከተዘጋጁት ችግኞች መካከል የኮሶ፣ ግራር፣ ወይራ ፣ ጌሾ ፣ ብሳና ፣ ዋንዛ ፣ ባህር ዛፍ ፣ የጽድና ሌሎች የደንና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚገኙበት አስረድተዋል። በተጨማሪም የሙዝ፣ አቮካዶ ፣ ማንጎ ፣ ፓፓያና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች መኖራቸውን ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅትም አርሶ አደሩ የሚተከሉ ችግኞች ጠቀሜታን በመገንዘቡ በግልና በማህበር ችግኞችን ማዘጋጀት መጀመሩንም ገልፀዋል። በዞኑ የአዋበል ወረዳ የወጀል ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መልሰው ገናነው እንደገለጹት፤ የችግኝ ተከላው የአካባቢ መራቆትን ከመታደግ ባሻገር የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ እያስቻለን ነው ብለዋል። አሁን ላይ ጥቅሙን በመገንዘባቸው በክረምቱ በግልና በህብረት ችግኞች ለመትከል መዘጋጀታቸውንም ነው የተናገሩት። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞች ውጤታማ እንዲሆኑ የድርሻቸውን እየተወጡ እንደሚገኙ የገለጹት ደግሞ በዞኑ የአነደድ ወረዳ የጉዳለማ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ተሻለ ጌታሁን ናቸው። ካለፉት ዓመታት ባገኙት ልምድ በመነሳትም በክረምቱ የሚተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ የጽደቀት መጠናቸው እንዲጨምር እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ የከተሞች የፋይናንስ ድጋፍ ጥምረትን ተቀላቀለች
Jun 23, 2026 1013
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ጥራትን ለማሻሻል እና የማህበረሰብ ጤናን ለመጠበቅ ለሚከናወኑ ስራዎች የፋይናንስ ድጋፍ የሚደረግበትን “የብሪዝ ሲቲስ ኔትወርክ” በአባልነት ተቀላቅላለች። የለንደን የአየር ንብረት ለውጥ ትግበራ ሳምንት መካሄዱን ቀጥሏል። በዛሬው ስብስባ ላይ አዲስ አበባ የ”ብሪዝ ሲቲስ” ከተሞች አባል መሆኗ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ በብሉምበርግ ግብረ ሠናይ የድርጅት፣ “በክሊን ኤር ፈንድ” እና “በሲ40 ሲቲስ” አማካኝነት ድጋፍ ይደረግለታል። ብሉምበርግ የተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት፣ የአየር ጥራትን ለማሻሻል 45 ሚሊዮን ዶላር በመመደብ በዓለም ላይ ከተመረጡ ከተሞች ጋር በትብብር የሚሰራበትን ፕሮግራም ይፋ አድርጓል። አላማውም የመዲናዋን የአየር ጥራት ለማሻሻልና ከአየር ጥራት ጋር ተያይዞ የሚመጣውን የጤና ጉዳት ለመቀነስ ያለመ ነው። ይኽም አዲስ አበባን ጨምሮ በ16 ዓለም አቀፍ ከተሞች የሚተገበር ይሆናል። የፕሮግራሙ ይፋ መሆን ተከትሎ፥ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተወካያቸው በኩል ባስተላለፉት መልዕክት አዲስ አበባ የብሪዝ ሲቲ አባል መሆኗ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ እያሳየ ያለውን ሁለንተናዊ የላቀ የከተማ ትራንስፎርሜሽን፤ ፅዱ፣ ውብ፣ አረንጓዴ እና ለመኖር ምቹ ከባቢን ከመፍጠር ስራ ጎን-ለጎን የአረንጓዴ አሻራ፣ የብስክሌት መንገድ እና የአየር ጥራት መቆጣጠርያ መሳሪያዎችን የበለጠ አስፋፍቶ እና አጠናክሮ ለመስራት ያግዛል ብለዋል። በቀድሞው የኒውዮርክ ከንቲባ ማይክል ብሉምበርግ በሚመሩት የግብረ ሰናይ ድርጅት እየተደረገ ያለው እገዛም የተጀመረውን ስራ አጠናክሮ ለመስራት እንደሚያስችል አመልክተዋል። በተጨማሪም ፕሮግራሙ አዲስ አበባ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ስታዘጋጅ በአየር ጥራት ቁጥጥር እና የአየር ጥራትን ማሻሻል የሚያስችሉ ተሞክሮዎችን ለሌሎች የአፍሪካ ከተሞች ብሎም ለአለም አቀፍ ከተሞች ተሞክሮ ለማሳየት እንደሚያግዝ አመልክተዋል። የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ልዩ መልዕክተኛ እና የብሉምበርግ ግብረ ሰናይ ድርጅት ዋና መስራች ማይክል ብሉምበርግ በበኩላቸው፣ በብሪዝ ሲቲስ አማካኝነት የከተማ ከንቲባዎች እንዲሁም መሪዎች የአየር ጥራትን ከማሻሻል አንጻር ግንባር ቀደም ሆነው መስራት መቀጠላቸውን ገልጸዋል። እያንዳንዱ ከተማ ወደፊት የአየር ጥራትን ከማሻሻል አንጻር የሚወስደው እርምጃ ሕይወትን ለማዳን፣ የሕዝብ ጤናን ለማሻሻል እና የብክለትን ልቀትን ለመቀነስ እንደሚረዳ ጠቅሰው፤ ይህም ከተሞችን ለመኖርና ለመሥራት የተሻሉ ቦታዎች እንደሚያደርጋቸው ተናግረዋል። ይህ አዲስ ኢንቨስትመንት ወይም ድጋፍ ከንቲባዎች እያደረጉ ባለው ስራ ተጨማሪ እገዛ ያደርጋል፤ ከነዚህ ስራዎች የሚገኙ ተሞክሮዎችንም ወደ ተጨማሪ ከተሞች ለማድረስ ያግዛል ብለዋል። ዛሬ ከተቀላቀሉት አዲስ አበባ እና ማድሪድ ከተሞች በተጨማሪ፥ አክራ፣ ባንኮክ፣ ቦጎታ፣ ብራስልስ፣ ጃካርታ፣ ጆሃንስበርግ፣ ለንደን፣ ሜክሲኮ ሲቲ፣ ሚላን፣ ናይሮቢ፣ ፓሪስ፣ ሪዮ ዴ ጄኔሮ፣ ሶፊያ፣ እና ዋርሶ የብሪስ ሲቲስ ፕሮግራም ተጠቃሚ ከተሞች ናቸው። ይህም ብክለትን ለመቀነስ እና የህዝብ ጤናን ለማሻሻል የሚሰሩ ከንቲባዎችን ትብብር ለማጠናከር የጎላ ፋይዳ እንዳለው ተመላክቷል። ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው የለንደን የአየር ንብረት ለውጥ ትግበራ ሳምንት እስከ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 11700
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 8504
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 7324
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 7223
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል
Jun 23, 2026 1424
በኢዜአ ዐይን…! በዮሐንስ ደርበው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ጥቅም ንጥልም ቀላልም አይደለም፤ በተለያዩ ዐውዶች ገዝፎ ይገለጣል እንጅ። ለአብነትም፤ የደን ሽፋንን በማሳደግ የዓየር ንብረት ተጽዕኖን በመቀነስ ብሎም በመከላከል፣ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ እንዲሁም በመከላከል ምርታማነትን በመጨመር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የከተማ ውበት መጠበቅን ጨምሮ የተለያዩ ጥቅሞችን በቀጥታ ለሰው ልጆች ይቸራል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ አረንጓዴ ዐሻራ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልጽግና አሠናሥሎ የሚያረጋግጥ ብሔራዊ ኢኒሼቲቭ ነው። የደን፣ የሰብልና ሁለንተናዊ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ወሳኝ የልማት አቅጣጫም ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት ጽንሰ ሐሳቡ ከችግኝ ተከላ የተሻገረው አረጓዴ ዐሻራ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ መነሻ፤ የተራቆተ አካባቢን ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ከማድረግ የላቀ ድርብርብ ግብ ያለው ሰፊ መርሐ-ግብር ነው። በዚህም መሠረት፤ እንደየ ሥነ-ምኅዳሩ የሚላመዱ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ላላቸው ችግኞች፣ ለደን ሽፋን ማደግ የጎላ ሚና ለሚኖራቸው ችግኞች፣ ለከተማ ውበትና ለማረፊያ ጥላ ለሚሆኑ ዛፎች፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የሚችሉ ዛፎች የሚተከሉበት ነው። ይህም አንድን አካባቢ አረንጓዴ ከማድረግ ልቆ በረሃማነትንና የዓየር ንብረት ተጽዕኖን በመቀነስ፣ ምርታማነትን በመጨመር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን በማሳደግ በቀጥታ ሕብረተሰቡን የሚጠቅም ትልቅ ኢኒሼቲቭ መሆኑን ያስረዳል። የተለያዩ ክፍላተ-ዓለማት አንድም በካፋ ቅዝቃዜ እንዲሁም መደበኛ የኑሮ ሁኔታን በሚያናጋ አደገኛ ሙቀት ብሎም በድንገተኛ ጎርፍ እና ሰደድ እሳት በሚታመሱበት ጊዜ፤ እነዚህንና መሰል ችግሮችን ቀድሞ ለማረቅ አንዱ መፍትሔ አረንጓዴ ዐሻራን በስፋት ማከናወን መሆኑ ይታመናል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነትና ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባለፉት ዓመታት በብርቱዎቹ ኢትዮጵያውያን ርብርብ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል፤ ውጤቱንም ሕዝቡ ዐይቷል። ከውጤቶቹ መከካልም ለአብነት፤ ከሀገራዊ ለውጡ በፊት 17 ነጥብ 2 በመቶ የነበረው የደን ሽፋን አሁን ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማደጉ፣ የምርታማነትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት መጨመር ብሎም ውብና አረንጓዴ ከተሞች መስፋፋት የሚሉት ይነሳሉ። በሕዝቡ ዘንድ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ተፈጥሮን የመንከባከብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የሀገርን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጉዳይ ጭምር ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል። የአረንጓዴ ዐሻራን ውጤት ላጣጣመ ሥራውን በንቃት እንዲከውን መካሪ ባያሻም፤ ካለፈው የበለጠ ውጤት እንዲገኝ ዛሬ ላይ ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚነታቸውን በሚያረጋግጠው የአረንጓዴ ዐሻራ በነቂስ መሳተፍ እና ባሕላቸው ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ከአረንጓዴ ዐሻራ ትሩፋቶች መካከል • በሰብል፣ ፍራፍሬ፣ ቡና ምርታማነት እና በሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን ያደረገው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ አሁን ዘርፈ-ብዙ ጥቅሙ በተጨባጭ እየተገለጠ ነው። ከበርካታ ትሩፋቶቹ መካከልም የምርታማነት ማደግ ተጠቃሽ ነው። ይህን ተከትሎም የሕብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አድጓል። ይህን ሐሳብ በአኃዝ አስደግፎ ብናየው፤ ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፊት (በ2010 ዓ.ም) በሔክታር የሚመረተው ስንዴ 22 ኩንታል፣ በቆሎ 30 ኩንታል፣ ጤፍ 17 ኩንታል እንዲሁም ገብስ 23 ኩንታል ነበር። ከኢንሼቲቩ ትግበራ በኋላ ደግሞ (በ2017 ዓ.ም) ስንዴ በሔክታር 36 ኩንታል፣ በቆሎ 46 ኩንታል፣ ጤፍ 20 ኩንታል፣ ገብስ 30 ኩንታል ማምረት ተችሏል። በዚህም መሠረት በ2017 ዓ.ም 7 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር መሬት በስንዴ ሰብል በመሸፈን 280 ሚሊየን ኩንታል ማምረት ተችሏል። ስንዴን በትጋት በማምረትም ከውጭ ለማስገባት ይወጣ የነበረን 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል። በሌላ በኩል ደግሞ፤ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፍራፍሬው ዘርፍ ዕድገትም ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል። በዚህም ገበያውን ከማረጋጋት ባለፈ ሕብረተሰቡ (አምራቹ) ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ በዚያው ልክ እንዲያድግ አስችሏል። ኢትዮጵያም በአፍሪካ አቮካዶን በቀዳሚነት ወደ ውጭ የምትልክ ሁለተኛዋ ሀገር እንድትሆን አስችሏታል። ሌላኛው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ትሩፋት የቡና ልማት መስፋፋትና የውጭ ምንዛሬ ማደግ ነው። ይህን በአሥረጂ አስደግፈን ብንመለከት፤ በ2011 ዓ.ም በ600 ሺህ ሔክታር ላይ ቡና ተተክሏል። 500 ሺህ ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል። 738 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኝቷል። እንዲሁም በ2017 ዓ.ም 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ቡና ተተክሏል። 1 ነጥብ 58 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል። 2 ነጥብ 65 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢም ማግኘት ተችሏል። እንዲሁም ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ጋር በተያያዘ ለ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል። ከላይ የተጠቀሱ ማሳያዎችን (ናሙናዎችን) ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በቀጥታ ለሕዝቡ ጥቅም የቆመ መርሐ-ግብር መሆኑን መገንዘብ አያዳግትም። ስለዚህ በቀጣይ ሕብረተሰቡ በዚህ ኢኒሼቲቭ ላይ ያለጠባቂነት በንቃት በመሳተፍ እና ባሕሉ በማድረግ ተጠቃሚነቱንም በዚያው ልክ ለማሳደግ መትጋት ይጠበቅበታል። እስከ ዓለም ከፍታ ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር የሚዳርገው ህመም ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ አበርክቶዎች መካከል • በመሬት መራቆት መቀነስ፣ በደን ሽፋን ማደግ፣ በውኃማ አካላት መስፋፋት ረገድ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ፤ የአካባቢ መራቆትን በመቀነስና በመቅረፍ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል፣ በደን መጨፍጨፍ ምክንያት ይከሰት የነበረን የበረሃማነት መስፋፋት ቀንሷል፣ የደን ሽፋንን ጨምሯል፣ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ መሬት እንዲያገግም በማድረግ ምርታማነትን ጨምሯል። በተጨማሪም የውኃማ አካላትን መመናመን ቀንሷል (ደርቀው የነበሩ ስፍራዎች ወደ ቀድሞ ውኃማ ይዘታቸው እንዲመለሱ አስችሏል)፣ የአካባቢ መራቆትና የዓየር ንብረት ፈተናዎችን በመቀነስ ረገድም የራሱን ከፍተኛ ሚና አበርክቷል። ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ትግበራዋ ስኬታማነት ዓለም ዕውቅና ችሯታል በሀገር አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማትና መሪዎች ዘንድ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ትግበራ ተወድሷል። ከእነዚህ ዕውቅናዎች መካከል፤ የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአግሪኮል ሽልማት መስጠቱ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) Outstanding African Leadership Award ማግኘታቸው የሚሉት ይጠቀሳሉ። እንዲሁም፤ ኢትዮጵያ 2ኛውን የአፍሪካ የዓየር ንብረት ጉባዔ ተመርጣ ማስተናገዷ፣ ኢትዮጵያ 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት የሥርዓተ-ምግብ ጉባዔ ማስተናገዷ፣ በ80ኛው የዓለም ምግብና እርሻ ድርጅት ጉባዔ ለዘላቂ ደን ልማት የተሰጣት ዕውቅና እንዲሁም ኢትዮጵያ ኮፕ-32 (COP- 32) ለማስተናገድ መመረጧ በዘርፉ ላከናወነችው አርዓያነት ያለው ተግባር የተሰጡ ዕውቅናዎች ናቸው። ኢትዮጵያ ስኬታማውን የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ትልሟን ለሀገራት ማጋራቷ ኢትዮጵያ በራሷ ሐሳብ አመንጭነት ሕዝቧን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እየተሰጠ ባለ ያልተቆራረጠ ጠንካራ አመራር በአረንጓዴ ዐሻራ ዘርፍ ያስመዘገበችውን ስኬት፣ አሠራር (ልምድ) እና ችግኝ ለተለያዩ ሀገራት አጋርታለች። ይህም እየሄድችበት ያለው መንገድ ሁሉ ተባብሮ ማደግን ያነገበ ለመሆኑ አሥረጂ ነው። በዚህም መሠረት፤ በ2012 ዓ.ም ለፑንትላንድ፣ በ2012 ዓ.ም ለፓኪስታን፣ በ2012 ዓ.ም ለጂቡቲ፣ በ2013 ዓ.ም ለደቡብ ሱዳን፣ በ2013 ዓ.ም ለሩዋንዳ እና ለሌሎችም በዘርፉ ያላትን የተመሠገነ ልምድ አጋርታለች። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ የተመራበት ሂደት የኢኒሼቲቩ ሐሳብ አመንጭ እና አመራር ሰጭ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ናቸው። ወደ ክልል፣ ዞን ወረዳ እና ቀበሌ በማውረድም በተቀናጀ ትጋት በመመራቱም ስኬታማ መሆን ችሏል። በዚህም መሠረት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነትና አመራር ሰጭነት፣ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች እና ባለድርሻ አካላት ቅንጅት፣ በክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮችና ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ቅንጅት፣ በየደረጃው በተዋቀረ የቴክኒክ ኮሚቴ አማካኝነት፣ በተደራጀ የሕዝብ ተሳትፎ አማካኝነት የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በስኬት እየተተገበረ ይገኛል። ከአረንጓዴ ዐሻራ ጋር በተያያዘዘ የቀጣይ አቅጣጫዎች የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ የለውጡ መንግሥት ከመጣ ወዲህ ላለፉት ዓመታት በተቀናጀ አግባብ ተመርቷል፤ አሁንም እየተተገበረ ነው። በቀጣይ ደግሞ ኢኒሼቲቩ እንዴት መከናወን እንዳለበት ግቦች ተቀምጠዋል። በዚህም መሠረት፤ የሕዝብ ባለቤትነትን አጠናክሮ ማስቀጠል (አረንጓዴ ባሕል መገንባት)፣ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎችን ማስፋትና በደን ላይ የሚደርሰውን ጫና መቀነስ፣ የሕግና የፖሊሲ ማሻሻያ የሚፈልጉ ጉዳዮችን ለይቶ በጥናት መመለስ የሚሉት የቀጣይ አቅጣጫዎች ናቸው። በተጨማሪም፤ ከአረንጓዴ ዐሻራ የሚገኘውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት አጠናክሮ ማስቀጠል፣ የባለድርሻ አካላት እና የተቋማት ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር፣ በክረምት ወራት የሚተከሉ ችግኞችን በበጋ ወራት በአግባቡ መንከባከብ ከቀጣይ አቅጣጫዎች መካከል ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በቢሾፍቱ ማስጀመራቸው ይታወቃል። በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክትም፤ ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞች ለተከላ ዝግጁ በሆኑበት በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ወቅት አረንጓዴ ለሆነች ነገ፣ ሁላችንም ተስፋን እንትከል ሲሉ ለሀገሬው ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ዘርፈ-ብዙ ጥቅሙ በተጨባጭ እየተገለጠ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2011 ዓ.ም መጀመሩም የሚታወስ ነው። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #ተስፋን_እንትከል
ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes)
Jun 23, 2026 793
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው · ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ሕጻናት ላይ የትኛው የስኳር ህመም ነው በስፋት እየተከሰተ ያለው? በሕጻናት ላይ የሚከሰቱ የተለያዩ የስኳር ህመም ዓይነቶች መኖራቸውን የሚገልጹት የሕጻናት የስኳር ህመም ስፔሻሊስት ዶክተር ሰውአገኝ የሺዋስ፤ እንደሀገራችን ግን በዋናነት የሚጠቀሰው ዓይነት አንድ የሚባለው የስኳር ህመም ነው ይላሉ። በአደጉ ሀገራት ላይ ዓይነት ሁለት የስኳር ህመምም በሕጻናት ላይ እንደሚከሰት ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም ባብዛኛው እንቅስቃሴ ካለማድረግ፣ ከኑሮ ዘይቤ እንዲሁም ከመጠን ባለፈ ውፍረትና ተያያዥ ጉዳዮች ምክንያት የሚከሰት መሆኑንም ያስረዳሉ። ይሁን እንጅ በእኛ ሀገር ደረጃ ይህ (ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም) በስፋት በሕጻናት ላይ እንደማይስተዋልና ብዙም አሳሳቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። በዋናነት በእኛ ሀገር ሕጻናት ላይ እየተከሰተ ያለው ዓይነት አንድ የስኳር ህመም መሆኑን ገልጸው፤ተገቢው ጥንቃቄ ባለመደረጉ ልጆች ለውስብስብ ችግር እየተዳረጉ ነው ብለዋል። እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የጡት ካንሰርን ለመከላከል ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? · ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም አጋላጭ ምክንያቱ ይታወቃል? እንደ ባለሙያው ገላጸ፤ ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም አጋላጭ መንስዔው አይታወቅም። ይህን ተከትሎም አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል ሕክምና የለም። እንደ አጋላጭ ከሚታሰቡት መከካል ግን፤ ልጆች በተፈጥሮ ለዓይነት አንድ የስኳር ህመም የመጋለጥ ዕድላቸው ከፍተኛ መሆኑ እና ውጫው (አካባቢያዊ ሁኔታዎች) በምክንያትነት ይነሳሉ ብለዋል። በእነዚህ ምክንያቶች በእያንዳንዱ የሰውነት እንቅስቃሴ ውስጥ ስኳር እንዲዋሃድ የሚያደርገው ኢንሱሊን የተሰኘ ሆርሞን መመረቱ ይቆማል፤ የኢንሱሊን እጥረት ሲያጋጥም ደግሞ ስኳር ደም ላይ እየጨመረ ይሄዳል፤ ደም ከ180 በላይ ከፍ በጊዜም ኩላሊት ወደ ውጭ ያስወግደዋል፤ በዚሁ ወቅትም ጠቃሚ ንጥረ ቅመሞች ጭምር ከሰውነት ይወገዳሉ፤ የፈሳሽ እጥረትም ያጋጥማቸዋል፤ ከዚያም የልጆች የሰውነት ክብደት መቀነስና ቶሎ ቶሎ (ከመደበኛው የተለየ) የመሽናት ሁኔታ ይከሰታል ሲሉ አብራርተዋል። · ዓይነት አንድና ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም እንደ ዶክተር ሰዋገኝ ማብራሪያ፤ ዓይነት አንድ እና ዓይነት ሁለት የስኳር ህመሞች የተለያዩ ናቸው። ዓይነት አንድ የስኳር ህመም ማለት፤ ኢንሱሊን በሰውነት ውስጥ ሳይመነጭ ሲቀር የሚከሰት መሆኑን አስረድተዋል። ይህን ህመም ቀድሞ መከላከል አይቻልም፤ ሲከሰት ሕክምና ማግኘት እንጅ ይላሉ። ዓይነት ሁለት የስኳር ህመም፤ ኢንሱሊን የማመንጨት ችግር ሳይሆን፤ ኢንሱሊኑ በሰውነት ውስጥ ሳይሠራ ሲቀር የሚከሰት ነው ይላሉ። ይህም ከሰውነት ክብደት መጨመር፣ አካላዊ እንቅስቃሴ ባለማድረግ ምክንያት የሚመጣ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲውም ብዙ ጊዜ በዐዋቂዎች ዘንድ በስፋት የሚስተዋል ህመም መሆኑንም አመላክተዋል። ይህን ህመም አመጋገብን በማስተካከል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ፣ የኑሮ ዘይቤን በማስተከከል ቀድሞ መከላከል እንደሚቻልም ነው ያስገነዘቡት። · የስኳር ህመም በየትኛው የዕድሜ ክልል ይከሰታል? ዓይነት አንድ የስኳር ህመም የ6 ወር ዕድሜ ካለው ሕጻን ጀምሮ እስከ በዐዋቂነት የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ዶክተር ሰውአገኝ ይናገራሉ። ይህን ሲያብራሩም በተለይም ከ30 ዓመት በታች ባሉት የዕድሜ ክልሎች (በተለይም ከ5 - 7 እንዲሁም ከ14 - 15 ዓመት) ባሉ ልጆች ላይ በስፋት ከሰታል ብለዋል። · ምልክቶቹ በውል ይታወቃሉ? በአብዛኛው ከተለመዱ ምልክቶች መካከል፤ ቶሎ ቶሎ ውኃ መጠጣት፣ የማይረካ የውኃ ጥማት መኖር፣ ከወትሮው የተለየ ሌሊትን ጨምሮ ሽንት የመሽናት፣ ክብደት መቀነስ የሚሉት እንደሚገኙበት ይገልጻሉ። እነዚህ ምልክቶች ሲታዩም ጊዜ ሳያባክኑ (ህመሙ ሥር ሳይሰድ) ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ ተገቢ መሆኑን መክረዋል። በዚህ ሂደት ልጆች ህመማቸውን ዐውቀውና ራሳቸውን ችለው ወደ ሕክምና ተቋም እንደማይሄዱ ስለሚታወቅ ወላጆች (አሳዲዎች) ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ሾተላይን ቀድሞ መከላከል ይቻላል? · ሕክምና እና ምክረ ሐሳብ ምንም እንኳ አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል የታወቀ ነገር ባይኖርም ዓይነት አንድ የስኳር ህመም፤ ቶሎ ከታወቀና ሕክምና ከተደረገለት ልጆች እንደማንኛውም ጤናማ ልጅ ዕድገታቸው ይቀጥላል፣ ትምህርታቸውን መማር፣ ኑሯቸውን መቀጠል ይችላሉ። ልጆች በጊዜው (ህመሙ እንደተከሰተ ወዲያውኑ) ካልታከሙ ሕይዎታቸውን እስከማጣት የሚደርስ ውስብስብ ችግር የሚፈጥር መሆኑን ገልጸው፤ ወላጆች (አሳዳጊዎች) የልጆቻቸውን ጤና በአግባቡ እንዲከታተሉ መክረዋል።የተለየ ምልክት ሲያስተውሉም ወደ ሕክምና መሄድን መክረዋል። ምንም እንኳን አመጋገብን ማስተካከል ለጤና እንደ ግብዓት ተጠቃሚ መሆኑ ቢታመንም፤ ዓይነት አንድ የስኳር ህመምን በአመጋገብ ብቻ እናስተካክላለን በሚል መዘናጋት ተገቢ እንዳልሆነ ሕብረተሰቡ ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል። በአመጋገብ ብቻ እናስተካክላለን ማለት ቶሎ እንዳይታከሙ ጊዜ በማባከን የልጆችን ጤና በይበልጥ ማወሳሰብ በመሆኑ፤ አዋጩ መፍትሔ በሕክምና ኢንሱሊን መስጠት እና በተጨማሪ አመጋገብን ከኢንሱሊኑ ጋር ማጣጣም መሆኑን አስገንዝበዋል። #የጤና_ነገር #ኢዜአ #ኢንሱሊን #የስኳር_ህመም #ሕጻናት
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Jun 21, 2026 1162
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 14/2018 (ኢዜአ) ፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? በሳምንቱ ቢሾፍቱ አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከባሕር ጠለል በላይ በ1 ሺህ 910 ሜትር ከፍታ ላይ በምትገኘው ቢሾፍቱ ግንባታው በመከናወን ላይ ይገኛል። የኤርፖርቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ግዙፍ የልማት ፕሮጀክት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የቢሾፍቱ ኢርፖርት ኢትዮጵያን ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ማዕከላት ተርታ ለማሰለፍ የሚያስችል ታሪካዊ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ሳምንት ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በስፍራው በመገኘት የግንባታውን ሂደት የተመለከቱ ሲሆን ግንባታውን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅም ሌሊትና ቀን በከፍተኛ ጥረት እየተገነባ ይገኛል ብለዋል። በእለቱም የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በቢሾፍቱ ያስጀመሩ ሲሆን ዘንድሮ የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞች የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጎሮ ወረዳ በመገኘት የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያስጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክትም ሀገራችንን በጋራ ማንሳት የምንችለው አንዳችን ለሌላችን እጃችንን ስንዘረጋ ብቻ ነው! ስለሆነም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በዚህ ሥራ እንዲሳተፍ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል። የሀገር መከታና የህዝብ አለኝታ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የህዝብ ወገንተኝነቱንና እና አለኝታነቱን በተግባር ማሳየቱን ቀጥሎበታል። ሰራዊቱ በጦር ሜዳ ጠላትን ድል ከመንሳት ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ የሚወጣ ህዝባዊ ሰራዊት መሆኑን አሳይቷል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት 403ኛ መከታ ኮር የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ተላላቅ መርሃ ግብሮች ባከበረበት ወቅት በሰሜን ጎንደር ዞን የ"ጭና ሰማዕታት መታሰቢያ ጤና ጣቢያ" ገንብቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ አስረክቧል። በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሰራዊቱ የጀግንነት ታሪክ እንደ ውቅያኖስ የማይነጥፍ ከመሆኑም በላይ፣ በጭና ግንባር የተቀዳጀው ድል የጠላትን ፖለቲካዊና ወታደራዊ አቅም ሙሉ በሙሉ የሰበረ የድል ማህተም ነው ብለዋል። ለልማት- የሃይል አማራጭን ማስፋት በኢትዮጵያ ከከተማ እስከ ገጠር የተሰናሰለ የሃይል ልማትን በማስፋት አማራጭ የሃይል አቅርቦት ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዚህ ሳምንትም በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ ከ312 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያስችል የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ለመገንባት መሰረተ ድንጋይ ተቀምጧል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሡልጣን ወሊ (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጥረት በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ለዘላቂ ልማትና ለዜጎች ተጠቃሚነት የሃይል አማራጭን የማስፋት ስራ ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አንስተዋል። በምርታማነት የምግብ ስርዓት ችግርን መፍታት በኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ችግርን ለመፍታት እስከ ታችኛው መንግስታዊ መዋቅር ድረስ የሚዘልቁ የተለያዩ ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በዚሁ መሰረትም በምግብ ስርዓት አለመስተካከል የሚከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገልጿል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት በክልሉ ስርዓት ምግብ ሽግግርና የቀዳማዊ ልጅነት ልማት ፍኖተ ካርታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄዷል። የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ችግር ፈች ምርምር ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በምርምር ሥራዎችና በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጸውም በዚህ ሳምንት ነው። በዩኒቨርሲቲው በምርምር ፕሮጀክቶች እና በማህበረሰብ አገልግሎቶች የተከናወኑ ተግባራትን ለመገምግምና ቅንጅታዊ ሥራን ለማጠናከር ያለመ መድረክም አካሄዶ ነበር። መድረኩ በተለይ ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶችን እውን ለማድረግና ዓለም አቀፍ ዕድሎችን አስፍቶ ለመጠቀም የተመራማሪዎችን አቅም ማሳደግ ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ ከ84 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ 54 የምርምር ሥራዎችን እንዲሁም 70 የማህበረሰብ አገልግሎቶችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። በቀብሪ በያህ ከተማ የወጣቶች የልማት ተጠቃሚነት በሶማሌ ክልል የልማትና የምርታማነት አጀንዳዎች በውጤታማነት ቀጥለዋል። የወጣችንና አጠቃላይ የክልሉን ህዝብ የልማት ፍላጎት መሰረት አድርገው እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው። በዚሁ መሰረት በክልሉ ፋፈን ዞን ቀብሪ በያህ ከተማ በማህበር ተደራጅተው ሥራ የፈጠሩ ወጣቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። አብዲከሪን መሀመድ እና ጓደኞቹ በማህበር ተደራጅተው በዶሮ እርባታ በመሰማራት በሌማት ትሩፋት የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል። ሥራውን ከጀመሩ ወዲህ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ ለሌሎች ወገኖችም ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙ ይናገራሉ። እንደ አጠቃላይ በሶማሌ ክልል ሰው ተኮር የልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ ቀጥለዋል። የበጀት ክለሳ በዚሁ ሳምንት የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የ2018 የበጀት ዓመት የ11 ወራት እቅድ አፈጻጸም መነሻ በማድረግ የቀረበለት የበጀት ክለሳ አፅድቋል። ካቢኔው በክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አማካኝነት የቀረበለትን ከ301 ሚሊየን 693 ሺህ 178 ብር የበጀት ክለሳ ነው ተወያይቶ ያፀደቀው። የበጀት ክለሳው በተለይም የፊስካልና ፋይናንሻል አፈፃፀማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ፕሮጀክቶችን በመለየት የላቀ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ላላቸውና የበጀት እጥረት ላጋጠማቸው ጉዳዮች የሚውል ነው ተብሏል። የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኢትዮጵያ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮቿን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት ልትሰጠው እየተጋች ነው። ለዚህ ዋና ማሳያው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ነው። ማዕከሉ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን የተገነባውን ኮንታ መሶብ የአንድ ማዕከል መርቀው በይፋ አገልግሎት አስጀምረዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል በተበታተነ ሁኔታ ይሰጡ የነበሩ የመንግሥትና የማኅበራዊ አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር በማሰባሰብ ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው። የኮንታ ማዕከልም ሕዝቡ ከቢሮ ወደ ቢሮ በመዘዋወር የሚያጠፋውን ጊዜ፣ ወጪና እንግልት በእጅጉ በመቀነስ ጥራት ያለው፣ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት እንዲያገኙ ያግዛቸዋል ተብሏል። የስደተኞች መጠጊያ- ኢትዮጵያ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞች መጠጊያ የሆነችው ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የስደተኞች ቀን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ተከብሯል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ክልሉ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞችን ከመቀበል ባለፈ ስደተኞችን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በክልሉ አራት መጠለያ ጣቢያዎች ላይ ከ112 ሺህ በላይ ስደተኞች እንደሚገኙ ገልፀው፥ ስደተኞች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ጠንካራ መስተጋብር በመፍጠር በአብሮነት እየኖሩ ነው ብለዋል። ስደተኞች የውሃ፣ የትምህርት የጤናና ሌሎች የመሠረተ ልማቶችን ከተቀባዩ ማህበረሰብ እኩል ተጠቃሚ መሆናቸው የኢትዮጵያን ስደተኞች አያያዝ የተሻለ ተሞክሮ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ጋምቤላ የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አባላት በመጪው የህዝብ ውክልና ስራ ስምሪት ወቅት የሚያከናውኗቸውን ተግባራት በተመለከተ የኦሬንቴሽን ፕሮግራም አካሂዷል። የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ጁል ናንጋል፣ የህዝብ ውክልና ተግባር የምክር ቤት አባላት ዋና ሃላፊነት መሆኑን ገልፀው፣ አባላቱ ወደ ህዝቡ በመቅረብ የህብረተሰቡን ፍላጎት፣ ችግርና አስተያየት በአግባቡ በማሰባሰብ ለመንግስት አካላት ማድረስ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። ምክትል አፈ ጉባኤው እንዳሉት፣ የህዝብ ውክልና ስራ በዜጎችና በምክር ቤቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እና የህዝብ ተሳትፎን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ያለው በመሆኑ አባላቱ በተሰጣቸው ኃላፊነት ትጋትና ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበዋል። ድሬደዋ ድሬደዋ የመስኖ ግንባታ። 'በቆላማ አከባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም' በሁላሁሉል ገጠር ቀበሌ ውስጥ የከርሰ ምድር ውሃን በመጠቀም የተሰሩ የንፁህ መጠጥ ውሃና የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች፥ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) በተገኙበት ተመርቋል። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) እና የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ ግድቡን በመረቁበት ወቅት ከምንም በላይ ለሰው ልጆች ህይወት እጅግ አስፈላጊ የሆነውና፥ የአስተዳደራችን የገጠር ነዋሪ ህብረተሰብ መሠረታዊ ፍላጎትና የረጅም ዘመናት ምኞት የነበረውን፥ የውሃ ጥያቄ በጋራ ርብርብ መመለስ መቻል የሚሰጠው ደስታ እጅግ ልዩ ነው ብለዋል ከንቲባው። የድሬዳዋን ማህበረሰብ የምግብ ሉኣላዊነት የማረጋገጥ፣ አርሶአደሩ ነዋሪ ከራሱ አልፎ ለገበያ በማቅረብ ኑሮውን እንዲያሻሽል እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የመስኖ ልማት ሥራዎችን እንዲያከናውን በማገዝ ረገድ ቀጣይነት ያለው ስራ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። አፋር ሳምንቱ በአፋር ክልል በማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ ያሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ወጣቶች፣ ባህልና ስፖርት ቢሮ ያስታወቀበትም ነበር። የአፋር ክልል አብዛኛው ማህበረሰብ ከፊል አርብቶ አደርና አርብቶ አደር በመሆኑ፣ በየዓመቱ የሚከናወኑ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክፍተቶች ለመሙላት ትልቅ ሚና አላቸው። በተለይም የአየር ንብረት መለዋወጥ፣ የውሃ እጥረት እና አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎችን ተቋቁሞ ዘላቂ ልማት ለማምጣት የወጣቶችና የህብረተሰቡ የተቀናጀ አቅም ወሳኝ ግብዓት ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። ማጠቃለያ ሳምንቱ በሁሉም ክልሎች መደበኛ የልማት፣ የማህበራዊ እና የሰላም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው የቀጠሉበትም ነበር። በሁሉም ክልሎች የስድስተኛ እና ስምንተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተካሄዷል። በተመሳሳይ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ዝግጅት በሁሉም ክልሎች እየተከናወነ ይገኛል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jun 15, 2026 3013
በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 👉የተራሮች ስር ፈርጥ - ወልዲያ የዛሬው የወፍ በረር ምልከታችን የሚጀምረው የተራሮች ስር ፈርጥ በሆነችው ወልዲያ ከተማ በመገኘት ነው። ከደሴ በ120 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውና በረጃጅም ተራሮች የተከበበችው ወልዲያ ከተማ ከነበረችበት ጉስቁልና ወጥታ አሁን ላይ በውበት ፈክታ ትገኛለች። በሳምንቱ በዚህች ከተማ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኮሪደር ልማቷንና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፤ ተዘዋውረውም ጎብኝተዋል። በተለያዩ ታሪካዊና ባህላዊ ትውፊቶች ስሟ ጎልቶ የሚጠራው ወልዲያ እንደ ከዋክብት ፈክታ እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ገጠር ጭምር እየተስፋፉ መሆኑን አንስተው በቀጣይ ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ትገሰግሳለች ብለዋል። 👉የሸደር አዳሪ ትምህርት ቤት የሚቀጥለው መዳረሻችን በሶማሊ ክልል ፋፈን ዞን አውበሬ ወረዳ ሼደር ከተማ አዲስ የተገነባውን አዳሪ ትምህርት ቤት መመረቅ ይሆኗል። የትምህርት ቤቱን ግንባታ መርቀው ስራ ያስጀመሩት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ናቸው። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸው፤ በክልሉ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋት የተማረ ትውልድ ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በ138 ሚሊየን ብር የተገነባው ዘመናዊ ትምህርት ቤት ስራ መጀመሩ ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል። 👉የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የበረራ ቅኝታችን ቀጥሎ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በመስኖ እየለማ ያለ የስንዴ ምርት የመጎብኘት እድል አግኝተናል። በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በ21 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የመስኖ ስንዴ ሰብል መሰብሰብ ተጀምሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የበጋ መስኖ ልማት ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም የአርሶ አደሩን ገቢ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። የግብርና ሜካናይዜሽንን በስፋት በመጠቀም እንዲሁም ፈጠራን በማከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ጥረቱ በተሳካ መልኩ መቀጠሉን አንስተዋል። 👉ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ዓለም አቀፍ ክስተት ነው። ችግሩ በተለይም በታዳጊ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ሰብአዊ ጉዳቶችን እያስከተለ ይገኛል። ኢትዮጵያም የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደመሆኗ መጠን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ መፍትሄ ለመስጠት ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች። በዚህ ረገድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት በሚከናወኑ ሥራዎች በምርምር እያገዙ ናቸው። በሂደቱ ውጤታማነት ላይ የሚመክር መድረክ በሰመራ በተደረገበት ወቅት የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች ችግሩን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት በምርምርና በማማከር እያገዙ መሆናቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የሰዎች ህገወጥ ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የነፃ የሕግ ድጋፍና የማማከር አገልግሎትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ለህብረተሰቡ እየሰጡ ናቸው። 👉የኢትዮጵያ እያመረተች ነው በአማራ ክልል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር «ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሃ ግብሩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እና ሌሎችም በተገኙበት ተካሂዷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የገቢ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ ለውጭ ምንዛሬ አይነተኛ የገቢ ምንጭ መሆን አስችሏል ብለዋል። 👉መሶብ በአርባ ምንጭ፣ ዲላ እና ነቀምቴ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች እየተስፋፋ የመጣው የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት በዚህ ሳምንት አርባ ምንጭ፣ እና ዲላ ከተሞች ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። የመሶብ ማእከላቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀዋል። የዲጅታል አሰራርን በማስፋት ለዜጎች ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። 👉ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ በመጠለያ የሚገኙ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩ ስለመሆኑ ያነሳል። በመሆኑም ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን አደራጅቷል። በመሆኑም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በእለቱ ድምፅ መስጠት ካልቻሉት መካከል የሰሜን ምስራቅ ዕዝ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀናት በፊት ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፃቸውን ሰጥተዋል። በተመሳሳይ በአፋር ክልል እና በደብረ ብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያዎች የሚገኙ ዜጎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል። 👉የመኸር እርሻ ንቅናቄ በሲዳማ ክልል የመኸር እርሻን በንቅናቄ በመምራት የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡና ገበያን የሚያረጋጉ የግብርና ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በንቅናቄ መድረኩ ርእሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት መሬት ጦሙን እንዳያድርና ግብአትን በወቅቱ በማቅረብ እንዲሁም ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት በመስጠት ምርታማነቱን ማሳካት አስችሏል። ዘንድሮም ተግባሩን በማስቀጠል የበልግ ሰብልን ከመሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻን ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። ይህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፍ በማምረት ገበያን ለማረጋጋትና ለኢንደስትሪዎች ግብአት ለማቅረብ ያስችላል ነው የተባለው። በምርት ዘመኑ የተያዘውን እቅድ ለማሳካትም አመራሩ ህብረተሰቡን በማስተባበር ለውጤቱ መትጋት እንዳለበትም በውይይቱ ተነስቷል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምርጥ ዘር ብዜትን በዓይነት፣ በመጠንና በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ ተችሏል። ቢሮው በግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ እና በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የዘር ብዜት ዕቅድ አፈጻጸምና ዝግጅት ላይ ያተኮረ የባለ ድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ እንደገለጹት፤ በክልሉ የምርጥ ዘርን በጥራትና በመጠን ለአርሶ አደሩ በወቅቱ በማድረስ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል። ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ ለኢንዱስትሪዎች በቂ ግብዓትን ለማቅረብና የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር አግዟል። ተግባሩን በማስቀጠልም በ2017/18 የምርት ዘመን በክልሉ ከ2 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ30 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ማምረት መቻሉንም ገልጸዋል።
ትንታኔዎች
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 514
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልየነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 3669
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ። ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…!
Jun 15, 2026 2093
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 7430
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 2871
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 16724
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 9799
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 15559
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
የሀዋሳ ቀጣይ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ
Jun 24, 2026 229
ሀዋሳ፤ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ቀጣይ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ በእንዳለ ደበላ (ሀዋሳ ኢዜአ) ታቦር ተራራን በአንድ ጎኗ አላሙራ ተራራን ደግሞ በሌላው ጎኗ ታቅፋ የከተመችው ሀዋሳ ከተማ የፍቅር ሐይቅን ጨምሮ የተለያዩ የመስህብ ስፍራዎችንም በጉያዋ አቅፋ ይዛለች። ለባህላዊ ሕክምና አገልግሎት ጭምር የሚውሉት የወንዶገነት እና የይርጋለም የተፈጥሮ ፍል ውሀዎች ከሀዋሳ በቅርብ ርቀት ላይ መገኘታቸው ከተማዋ የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን በማድረግ በኩል የራሳቸው አስተዋጽኦ አላቸው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መዲናዋ ሀዋሳ ካሏት ተፈጥሯዊ የመስህብ ስፍራዎች በተጨማሪ የተለያዩ ባህላዊና ሀይማኖታዊ በዓላት በድምቀት የሚከበሩባት መሆኑም በጎብኚዎች ተመራጭ አድርጓታል። ሀዋሳ ባላት የተፈጥሮ ሀብት ላይ ተጨማሪ ውበትን ያላበሳት የኮሪደር ልማትም ከተማዋን ለኑሮ፣ ለሥራና ለኢንቨስትመንት ይበልጥ ምቹና ተመራጭ እያደረጋት ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወደከተማዋ የሚመጡ ጎብኚዎች ቁጥር እንዲበራከትና የቆይታ ጊዜያቸውንም እንዲያራዝሙ በማድረግ በኩል የኮሪደር ልማቱ አዎንታዊ ሚና መጫወት ጀምሯል። በከተማዋ ከሪፈራል ሰርክል እስከ መንቦ፣ ከሳውዝ ስፕሪንግ እስከ ፍቅር ሐይቅ፣ ከፍቅር ሐይቅ እስከ ሳውዝ ስታር ሆቴል የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች በተፈጥሮ የታደለችውን ሀዋሳን የበለጠ አድምቋታል። ውበቷን አጉልቶ ከማውጣት በተጨማሪ የከተማዋ ገቢ በማሳደግ በኩልም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው። የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን ምክትል ሀላፊና የደንበኞች አገልግሎት የታክሰ አሰባሰብ ዘርፍ ሀላፊ ወይዘሮ ሙላት ዮሴፍ በእዚህ ሀሳብ ይስማማሉ። እሳቸው እንዳሉት ባለፉት 11 ወራት በከተማዋ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል። አምና በተመሳሳይ ወቅት 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ እንደተሰበሰበ አስታውሰው የዘንድሮው 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ብልጫ አለው ብለዋል። ለገቢው መጨመር በምክንያትነት ከጠቀሷቸው አንዱ የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ የንግድ እንቅስቃሴውና የጎብኚው ቁጥር እያደገ መምጣት ነው። ይህን የከተማዋን የገቢ አቅም የበለጠ ለማሳደግ ያስችላል የተባለለት ተጨማሪ የኮሪደር ልማትም በአሁኑ ወቅት ሥራው ተጀምሯል። ከሳውዝ ስታር ሆቴል በቀድሞው መናኸሪያ እስከ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ አንዱ ሲሆን በፍጥነት ለማጠናቀቅም ታቅዶ እየተሰራ ነው። ሀዋሳ የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነቷልን ይበልጥ ለማሳደግ አሁንም በትጋት እየሰራች ነው፤ አሁንም ልማት ላይ ነች። ከከተማዋ መግቢያ የሐይቅ ዳርቻ ጀምሮ እስከ ታቦር ተራራ ድረስ 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የሐይቅ ዳርቻ ልማት ተጀምሯል። ይህም የከተማዋን እድገት ከማስቀጠል ባለፈ ይበልጥ የሚያደምቃት ነው። ተመራጭነቷነም ከፍ ያደርገዋል። በስድስት ወራት ውስጥ እንዲጠናቀቅ ታቅዶ ወደሥራ የተገባው የሐይቅ ዳርቻ የኮሪደር ልማት በመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራ የፍቅር ሐይቅ መግቢያ፣ አሞራ ገደል እና አሣ ገበያ አካባቢዎችን አካቶ የሚገነባ ነው። የሐይቅ ዳርቻ ልማቱ 60 ሜትር ወደ ሐይቁ ተገብቶ የሚከናወን ሲሆን ሰው ሰራሽ የውሀ ፏፏቴ፣ በሐይቁ ዳርቻ የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የተለያዩ ሱቆች፣ ሬስቶራንት፣ የመመልከቻ ማማዎች እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎችን አካቶ የሚሰራ ነው። ልማቱ ተጠናቆ ወደአገልግሎት ሲገባ በከተማዋ የቱሪዝም እንቅስቃሴ ላይ አዎንታዊ አበርክቶ ይኖረዋል። የከተማዋ የቱሪዝም መረጃ እንደሚያሳየው ካለፉት ዓመታት ወዲህ በሀዋሳ ከተማ የቱሪስት ፍሰት እየጨመረ መጥቷል። በተለይ በኮንፈረንስ ቱሪዝም ረገድ እና በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በኩል እየታየ ያለው ለውጥ ከተማዋን በቱሪስቶች ይበልጥ ተመራጭ አድርጓታል። ሀዋሳ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ጨምሮ የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮችን ለማስተናገድ ተመራጭ መሆኗ በስፖርት ቱሪዝም ዘርፍ ይበልጥ እንድትታወቅ እያደረገ ነው። ክለባቸውን ለመደገፍ ወደከተማዋ የሚመጡ ደጋፊዎች ዘርፉ እንዲነቃቃ የራሳቸውን አሻራም እያሳረፉ ይገኛሉ። በሀዋሳ ከተማ የሚከበሩ ሀይማኖታዊና ባህላዊ በዓላትም ከተማዋ በርካታ እንግዶችን እንድታስተናግድ ከማድረጋቸው ባለፈ ለከተማዋ ገቢ መጨመር የራሳቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የዓለም ቅርስ ሆኖ የተመዘገበው የሲዳማ ዘመን መለወጫ በዓል (ፊቼ ጨምበላላ) ለእዚህ ጥሩ ምሳሌ ነው። የጎብኚዎችን ቀልብ የሚስበው ይሄ በዓል ሌላው የሀዋሳ ከተማ ድምቀት ነው። በየዓመቱ በፍቼ ጨምባላላ በዓል ላይ ለመታደም ከሀገር ውስጥና ከመላው ዓለም በርካቶች ወደሀዋሳ ከተማ ስለሚመጡ ዋነኛው የቱሪስት መስህብ ነው ማለት ይቻላል። እነዚህ ባህላዊ፣ ሀይማኖታዊና ተፈጥሯዊ እሴቶችን በአግባቡ በማልማትና በማጎልበት ሀዋሳን ይበልጥ የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በቅርቡ የግንባታ ሥራው የተጀመረው የሀዋሳ ፍቅር ሐይቅ ዳርቻ ልማት ለእዚህ አንድ ማሳያ ነው። ልማቱ ከተማዋን የሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ብሎም የዓለም ኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ትልቅ ራዕይ ይዞ የተጀመረ ነው። ይህን የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ የኮሪደር ልማት በይፋ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ናቸው። የፍቅርና የሕብር ተምሳሌት የሆነችውን ሀዋሳ ውበቷን ይበልጥ ለማውጣትና ተመራጭ ለማድረግ የክልሉ መንግስት አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። እንደእሳቸው ገለጻ የኮሪደር ልማት ሥራው በፍጥነት እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይም ከሀዋሳ ሐይቅ እስከ ሞኖፖል ድረስ ያለውን አካባቢ በአምስተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ለማልማት ታቅዷል። ሀዋሳን የኮንፈረንስ፣ የስፖርትና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ትልቅ ዕድል ይዞ ለሚመጣው የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ተናግረዋል። የሀዋሳ ከተማን በሀገር ውስጥና በአፍሪካ ተመራጭ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ እንደሚሰራ የገለጹት ደግሞ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ ናቸው። ከተማዋን ይበለጥ ተመራጭ ለማድረግ ለሚከናወነው የመጀመሪያ ዙር የሐይቅ ዳርቻ ልማት 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል። ከዚህ ውስጥ ደግሞ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን የሚሆው ከማህበረሰቡ የሚሰበሰብ መሆኑን ነው ከንቲባው የገለጹት። ህዝቡም የከተማዋን ልማት ለመደገፍ የአቅሙን እያገዘ ነው። ለልማቱ በአይነት፣ በገንዘብና በዕውቀት እያደረገ ያለው ድጋፍ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ከ1 ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጠር ያነሱት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሀዋሳ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ቸርነት ፍላቴ ናቸው። በሀዋሳ በተለያዩ ምዕራፎች የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እስካሁን ከ2ሺህ ለሚበልጡ ሰዎቸ የሥራ ዕድል በመፍጠር ለበርካቶች ተጨማሪ ጥቅምን አስገኝቷል። የልማት ሥራዎች ለከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ሀዋሳን ውብ፣ ምቹና ለኑሮ ተመራጭ ከተማ እያደረጓት በመሆኑ በቀጣይም ህብረተሰቡን በማሳተፍ ልማቱ እንደሚጠናከር ነው የገለጹት። ከታቦርና አላሙራ ተራሮች እግር ሥር የከተመችው ሀዋሳ ዛሬም በሥራ ላይ ናት፣ የሚሰሩ ልጇቿ ዛሬም ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ከተማዋን ይብልጥ ከፍ ለማድረግ እየታተሩ ነው። የከተማዋን የቀጣይ የዕድገትና የውበት ምዕራፏን እውን ለማድረግ ልጆቿ በአቅማቸው አሻራቸውን ለማሳረፍ ወደተግባራዊ ሥራ ገብተዋል። በማማዋ ላይ ከፍ ብላ ጎልታ እንድትታይ የሚያደርጉት ርብርብ በዚህ ከቀጠለ ራዕዩዋን በማሳካት ሀዋሳን ከሀገር ውስጥ ባለፈ የአፍሪካ ኮንፈረንስ ማዕከል የማድረግ ግብ መሳካቱ አይቀሬ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት
Jun 23, 2026 1026
በዮሐንስ ደርበው ከሰብል ልማት አኳያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጭነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን ያደረገው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ አሁን ዘርፈ-ብዙ ጥቅሙ በተጨባጭ እየተገለጠ ነው። ከበርካታ ትሩፋቶቹ መካከልም የምርታማነት ማደግ ተጠቃሽ ነው።ይህን ተከትሎም የሕብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አድጓል። ይህን ሐሳብ በአኃዝ አስደግፎ ለማየት ያህል፤ ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፊት (በ2010 ዓ.ም) በሔክታር የሚመረተው ስንዴ 22 ኩንታል፣በቆሎ 30 ኩንታል፣ ጤፍ 17 ኩንታል እንዲሁም ገብስ 23 ኩንታል ነበር። ከኢንሼቲቩ ትግበራ በኋላ ደግሞ (በ2017 ዓ.ም) ስንዴ በሔክታር 36 ኩንታል፣ በቆሎ 46 ኩንታል፣ ጤፍ 20 ኩንታል፣ ገብስ 30 ኩንታል ማምረት ተችሏል። በዚህም መሠረት በ2017 ዓ.ም 7 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር መሬት በስንዴ ሰብል በመሸፈን 280 ሚሊየን ኩንታል ማምረት ተችሏል። ስንዴን በትጋት በማምረትም ከውጭ ለማስገባት ይወጣ የነበረን 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል። በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ ከፍራፍሬ አኳያ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በፍራፍሬው ዘርፍ ዕድገትም ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል። በዚህም ገበያውን ከማረጋጋት ባለፈ ሕብረተሰቡ (አምራቹ) ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ በዚያው ልክ እንዲያድግ አስችሏል። ኢትዮጵያም በአፍሪካ አቮካዶን በቀዳሚነት ወደ ውጭ የምትልክ ሁለተኛዋ ሀገር እንድትሆን አስችሏታል። ከቡና ልማት መስፋፋት አኳያ ሌላኛው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በረከት የቡና ልማት መስፋፋትና የውጭ ምንዛሬ ማደግ ነው። ይህን በአሥረጂ አስደግፈን ብንመለከት፤ በ2011 ዓ.ም በ600 ሺህ ሔክታር ላይ ቡና ተተክሏል። 500 ሺህ ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል።738 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኝቷል። እንዲሁም በ2017 ዓ.ም 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ቡና ተተክሏል። 1 ነጥብ 58 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የቡና ምርት ተሰብስቧል። 2 ነጥብ 65 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ማግኘት ተችሏል። ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያ ከአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ጋር በተያያዘ ለ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል። ከላይ የተጠቀሱ ማሳያዎችን (ናሙናዎችን) ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ በቀጥታ ለሕዝቡ ጥቅም የቆመ መርሐ-ግብር መሆኑን መገንዘብ አያዳግትም። ስለዚህ በቀጣይ ሕብረተሰቡ በዚህ ኢኒሼቲቭ ላይ ያለጠባቂነት በንቃት በመሳተፍ እና ባሕሉ በማድረግ ተጠቃሚነቱንም በዚያው ልክ ለማሳደግ መትጋት ይጠበቅበታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በቢሾፍቱ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ባለፉት ዓመታት 48 ቢሊየን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፤ በዘንድሮው መርሐ-ግብር ደግሞ 8 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተቀምጧል። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #ተስፋን_እንትከል