ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በሲዳማ ክልል በበልግ እርሻ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት ተከናውነዋል - ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Jul 24, 2026 36
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በበልግ ወቅት እርሻ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳደሩን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች በሀዋሳ ዙሪያ፣ በደራራ፣ በብላቴ ዙሪያ እና በዳሌ ወረዳዎች በበልግ የለማ ማሳ የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንዳሉት በልግ አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች በበቆሎ፣ ቦሎቄና ሌሎች ሰብሎች የለማው ማሳ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል።   በምርት ወቅቱ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለግብአት አጠቃቀምና ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት ተሰጥቶ መከናወኑን ጠቁመዋል። በበልግ እርሻው ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት በመኽር ወቅትም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።   የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ ታምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ በበልግ እርሻ 152 ሺህ ሄክታር ማሳ በበቆሎ፣ ቦሎቄና ስራ ስር ሰብሎች መልማቱን ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥ 67 ሺህ ሄክታር የሚሆነው በበቆሎ መልማቱን ጠቁመው በምርት የተሸፈነውን ማሳ ውጤታማ ለማድረግም የእንክብካቤና የክትትል ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አመልክተዋል፡፡   የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አለማየሁ ዲጋ በበኩላቸው አንድ ሄክታር ማሳ ላይ ያለሙት በቆሎ በመልካም ቁመና ላይ መሆኑን ተናግረዋል። ከግብርና ባለሙያ በሚሰጣቸው ምክር በመታገዝ እርጥበትን በማሳ ውስጥ እንዲቆይ በማድረጋቸው የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ አመላክተዋል።   አርሶ አደር ጸሀይ በቀለ በበኩላቸው በማሳቸው ውስጥ እርጥበትን የማቆየት ስራ በመስራታቸው የበቆሎ ሰብላቸው በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በክልሉ የግብር አከፋፈል ስርአቱን ቀልጣፋና አስተማማኝ ለማድረግ እየተሰራ ነው
Jul 24, 2026 35
ባህርዳር፤ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የግብር አከፋፈል ስርአቱን በቴሌ ብር በማድረግ ቀልጣፋና አስተማማኝ ስርአት ለመዘርጋት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የግብር አከፋፈል ስርአቱን በቴሌ ብር ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ኢትዮ ቴሌኮም ጋር ዛሬ ማምሻውን ተፈራርሟል። የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ /ር) በወቅቱ እንደገለጹት፥ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ90 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ በራስ አቅም የመልማት ባህልን በማጎልበት አበረታች ውጤት ተገኝቷል። በአዲሱ በጀት ዓመትም የግብር ስርአቱን ዲጅታላይዝ በማድረግ ግልጽ፣ ቀልጣፋና ተአማኒነት ያለው የግብር ስርአት ለመገንባት ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲና ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የተደረሰው ስምምነትም ወደ ኢ-ታክስ ሲስተም የገቡ 420 ሺህ የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮችን ጨምሮ የደረጃ "ሀ" እና "ሐ" ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በቀላሉና በፍጥነት ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲከፍሉ የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪም የግብር ስርአቱን ተደራሽ ለማድረግና በዘርፉ የሚስተዋለውን ብልሹ አሰራር ለማስቀረት የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ችፍ የሞባይል ባንኪንግ ቢዝነስ ኦፊሰር አቶ ቡሩክ አዳነ በበኩላቸው፥ ከክልሉ ገቢዎች ቢሮ ጋር የተደረገው ስምምነት ዲጅታል 2030ን እውን ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል። ቢሮው ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ያበለጸገውን የኢ-ታክስ ሲስተም ከቴሌ ብር ጋር በማስተሳሰር ደንበኞች በቀላሉ ግብራቸውን የሚከፍሉበት ስርአት ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የግብር ክፍያውን በቴሌ ብር ለማድረግም በዩኒቨርሲቲው የበለጸገውን ሲስተም ከቴሌብር ጋር እንዲናበብ በማድረግ፣አሰራሩን በመፈተሽና የደህንነት ጉዳዮችን የማረጋገጥ ስራ ቀድሞ ማጠናቀቁን ተናግረዋል። ደንበኞችም ከገቢዎች ቢሮ የሚሰጠውን የመክፈያ ኮድ በማስገባት ግብራቸውን በቴሌብር በቀላሉ፣ በፍጥነትና አስተማማኝነት ባለው መንገድ እንዲከፍሉ የሚያስችል ነው ብለዋል። አያይዘውም ኩባንያው ቴሌብር የሚጠቀሙ ደንበኞችን ቁጥር 60 ነጥብ 5 ሚሊየን ማድረሱን ጠቁመው ባለፉት አምስት ዓመታትም 9 ትሪሊዮን የሚጠጋ የገንዘብ ዝውውር ማድረግ መቻሉን አውስተዋል። የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር፣ ምርምር፣ ማህብረሰብ አገልግሎትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ባሻገር ከተቋማት ጋር በቅንጅት ለሀገር እድገት የሚበጁ ተግባራትን አያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ከክልሉ ገቢዎች ቢሮ ጋር በመተባበርም የኢ-ታክስ ፕሮጀክትን በማልማት የዘርፉን ችግር ለመፍታት መስራቱን ጠቁመው፥ አሁን ላይ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የተደረሰው ስምምነት የኢ-ታክስ ሲስተሙን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ነው ሲሉ አክለዋል። ማምሻውን በተካሄደው ስምምነት ላይም የቢሮው የማኔጅመንት አበላት፣ የኢትዮ-ቴሌኮም የስራ ሃላፊዎች፣ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ተገኝተዋል።
ኮርፖሬሽኑ ያደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ለተከታታይ ዓመታት በውጤታማነት እንዲቀጥል አስችሎታል
Jul 24, 2026 43
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጡን መነሻ ያደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ለተከታታይ ዓመታት ውጤታማነቱ እንዲረጋገጥ እንዳስቻለው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ገለፀ። የኮርፖሬሽኑ በ2019 በጀት ዓመትም ይህንኑ አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ስትራቴጂካዊ አቅጣጫም ተቀምጧል። ኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ውይይቱን አካሂዷል። በዚህ የግምገማ መድረክ በበጀት ዓመቱ የተቀመጠውን ዕቅድ 97 በመቶ ማከናወን መቻሉ የተገለፀ ሲሆን፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በገቢ ዕድገት፣ በቤት ልማት፣ በመስፈጸም አቅም እና በቤት አስተዳደር ረገድ የተከናወኑት ሥራዎች የተቋሙን አጠቃላይ የለውጥ ጉዞ ማረጋገጣቸው ተጠቁሟል።   በተጨማሪም የሕዝብና የመንግስት ጥቅም ለማስጠበቅ በፍርድ ቤት በተከናወኑ ክርክሮች በርካታ ይዞታዎችን ማስመለስ ተችሏል ብሏል። ኮርፖሬሽኑ በምሥራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ገበያ ለመሰማራት ያስቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት፣ በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ልማት ለመሳተፍ ከደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያል ስቴት ጋር የተደረሰው ስምምነት ወደ ተግባር ለማስገባት ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ አስታውቋል። የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ የፒያሳ እና የጎልድ ሳይት ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ አገልግሎት ማስገባት የተቻለ ሲሆን፣ ዘመናዊ የ3ዲ የግንባታ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት የሚያስችሉ የመጀመሪያዎቹ የሙከራ ቤቶች ግንባታም በመከናወን ላይ ይገኛሉ። በሌላ በኩል የቤቶች ቆጠራና የመረጃ ማሰባሰብ ሥራ በመጠናቀቁ ዘመናዊ የቤት አስተዳደር ሥርዓትን ማጠናከር የተቻለ ሲሆን፣ በርካታ የንግድ ቤቶችም ከደንበኞች ጋር በትብብር ተገንብተው ወደ ኪራይ አገልግሎት በመግባታቸው ከፍተኛ ገቢ ማስገኘት ጀምረዋል። ከዚህ ባሻገር የተቋሙን የ50 ዓመት የጉዞ ታሪክና ስኬቶች የሚያስተዋውቁ የተለያዩ መርሐግብሮች በኢዮቤልዩ በዓሉ ወቅት ለአራት ተከታታይ ቀናት በታላቅ ድምቀት ተከብረዋል። በዚህም የተቋሙን ገጽታ መቀየር መቻሉም ነው የተገለጸው፡፡ በአዲሱ የ2019 በጀት ዓመት ዘመናዊና ፈጣን የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ሥራ ላይ ማዋል፣ የሀገር ውስጥ የቤት አቅርቦትን ለማሳደግ ሰፋፊ የቤት ልማት መርሐግብሮችን መተግበር፣ አዳዲስ አሰራሮችን በመጠቀም የገቢ ምንጮችንና የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋፋት እንዲሁም የሰው ኃይል እና የአሰራር ሥርዓት አቅምን ማጠናከር ዋነኛ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ሆነው ተቀምጠዋል። ኮርፖሬሽኑ በአዲሱ የበጀት ዓመት የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት ለአገራዊ የቤት ልማት ዕቅድ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል።
በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ የመግባባትና የአንድነት ታሪክ እየተጻፈ ነው
Jul 24, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ የመግባባትና የአንድነት ታሪክ እየተጻፈ መሆኑን ዑስታዝ ጀማል በሽር ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ለምክክር የቀረቡ ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በእነዚህ አጀንዳዎች ላይም 4ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ከሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተመካከሩ ይገኛሉ። ዑስታዝ ጀማል ለኢዜአ በሰጡት አስተያየትም፤ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ ታሪክ እየተጻፈበት መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ ቀደም በነበሩ ሥርዓቶች ውሳኔዎች ከላይ ወደ ሕዝብ የሚወርዱበት አሰራር እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ግን ሕዝቦች በመመካከር በጋራ ውሳኔ የሚደርሱበት አውድ ተፈጥሯል ብለዋል። የምክክር ጉባኤም ''ኢትዮጵያ እየመከረች ነው'' የሚለውን መሪ ሃሳብ በሚመጥን መልኩ በሕዝብ ወኪል በሆኑ ተመናካካሪዎች መካከል ግልፅና አሳታፊ ምክክር እየተደረገበት መሆኑን ገልጸዋል። ከሂደቱም የሚጠበቁ ምክረ ሀሳቦች ለኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና ዕድገት የሚያግዙ ውጤቶችን የሚያመጣ መሆኑን ተናግረዋል። በዓለም ላይ በምክክር ችግሮቻቸውን የፈቱ ሀገራት ብዙ ናቸው ያሉት ተመካካሪው፤ የምክክር ጉባኤውም በኢትዮጵያውያን ግልጽ ተሳትፎ መመራቱ ሀገራዊ መግባባትን መፍጠር እንደሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል። ከምክክሩ የሚወጡ ምክረ ሀሳቦች በባለድርሻ አካላት ተግባራዊ ሆነው የሕዝቦችን ተጠቃሚነትና የሀገርን የጋራ ጥቅም የሚያሳድጉ ውጤቶች እንደሚያመጡ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሀሳቦችን ወደ አንድ የጋራ መግባባት ለማምጣት የተከፈተ ታላቅ መድረክ መሆኑንም ተናግረዋል። በምክክር የሚገነባው መግባባትም ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና የጋራ ብልፅግና መሰረት እንደሚሆን አንስተዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ተግባራትን እያከናወነ ነው
Jul 24, 2026 63
ድሬደዋ፣ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦የድሬዳዋ አስተዳደር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህን ጨምሮ የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና ነዋሪዎች ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ንግስ በአል ድሬዳዋ ለመጡ ምዕመናንና እንግዶች አቀባበል አድርገዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በወቅቱ እንዳሉት፥ ከተማዋ በህብረ ብሔራዊ አንድነት የደመቀች በመሆኗ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለሚያጠናክሩ ተግባራት ትኩረት በመስጠት እየተከናወኑ ነው። ድሬዳዋ እንግዶችን በፍቅር የመቀበል ልምድ ያላት መሆኗም የዚሁ መገለጫ መሆኑን ጠቁመው የዛሬው አቀባበልም ይህንኑ በተግባር ያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማዋ የሰላም፣ የልማትና የፍቅር ተምሳሌት በመሆኗም ለኃይማኖታዊም ሆነ ሌሎች ሁነቶች ተመራጭነቷ እያደገ መምጣቱን አመልክተዋል። ድሬዳዋ የዜጎች የርስ በርስ ትስስር ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት መጠናከር መሰረት መሆኑን በተግባር አሳይታለች ያሉት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ በበኩላቸው መምሪያው የቁሉቢ ገብርኤል አመታዊ ንግስ በአል ታዳሚዎች በድሬዳዋ ቆይታቸው ሰላማዊ ጊዜ እንዲያሳልፉ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። ለኃይማኖታዊ ክብረ በአሉ ወደ ድሬዳዋ ከመጡ ምዕመናን መካከል አቶ ስዩም ታደሰ እና አቶ የፈቃዱ አስናቀ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና ነዋሪዎች ያደረጉላቸው አቀባበልና መስተንግዶ አስደስቷቸዋል።
የሚታይ
ኮርፖሬሽኑ ያደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ለተከታታይ ዓመታት በውጤታማነት እንዲቀጥል አስችሎታል
Jul 24, 2026 43
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጡን መነሻ ያደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ለተከታታይ ዓመታት ውጤታማነቱ እንዲረጋገጥ እንዳስቻለው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ገለፀ። የኮርፖሬሽኑ በ2019 በጀት ዓመትም ይህንኑ አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ስትራቴጂካዊ አቅጣጫም ተቀምጧል። ኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ውይይቱን አካሂዷል። በዚህ የግምገማ መድረክ በበጀት ዓመቱ የተቀመጠውን ዕቅድ 97 በመቶ ማከናወን መቻሉ የተገለፀ ሲሆን፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በገቢ ዕድገት፣ በቤት ልማት፣ በመስፈጸም አቅም እና በቤት አስተዳደር ረገድ የተከናወኑት ሥራዎች የተቋሙን አጠቃላይ የለውጥ ጉዞ ማረጋገጣቸው ተጠቁሟል።   በተጨማሪም የሕዝብና የመንግስት ጥቅም ለማስጠበቅ በፍርድ ቤት በተከናወኑ ክርክሮች በርካታ ይዞታዎችን ማስመለስ ተችሏል ብሏል። ኮርፖሬሽኑ በምሥራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ገበያ ለመሰማራት ያስቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት፣ በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ልማት ለመሳተፍ ከደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያል ስቴት ጋር የተደረሰው ስምምነት ወደ ተግባር ለማስገባት ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ አስታውቋል። የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ የፒያሳ እና የጎልድ ሳይት ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ አገልግሎት ማስገባት የተቻለ ሲሆን፣ ዘመናዊ የ3ዲ የግንባታ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት የሚያስችሉ የመጀመሪያዎቹ የሙከራ ቤቶች ግንባታም በመከናወን ላይ ይገኛሉ። በሌላ በኩል የቤቶች ቆጠራና የመረጃ ማሰባሰብ ሥራ በመጠናቀቁ ዘመናዊ የቤት አስተዳደር ሥርዓትን ማጠናከር የተቻለ ሲሆን፣ በርካታ የንግድ ቤቶችም ከደንበኞች ጋር በትብብር ተገንብተው ወደ ኪራይ አገልግሎት በመግባታቸው ከፍተኛ ገቢ ማስገኘት ጀምረዋል። ከዚህ ባሻገር የተቋሙን የ50 ዓመት የጉዞ ታሪክና ስኬቶች የሚያስተዋውቁ የተለያዩ መርሐግብሮች በኢዮቤልዩ በዓሉ ወቅት ለአራት ተከታታይ ቀናት በታላቅ ድምቀት ተከብረዋል። በዚህም የተቋሙን ገጽታ መቀየር መቻሉም ነው የተገለጸው፡፡ በአዲሱ የ2019 በጀት ዓመት ዘመናዊና ፈጣን የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ሥራ ላይ ማዋል፣ የሀገር ውስጥ የቤት አቅርቦትን ለማሳደግ ሰፋፊ የቤት ልማት መርሐግብሮችን መተግበር፣ አዳዲስ አሰራሮችን በመጠቀም የገቢ ምንጮችንና የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋፋት እንዲሁም የሰው ኃይል እና የአሰራር ሥርዓት አቅምን ማጠናከር ዋነኛ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ሆነው ተቀምጠዋል። ኮርፖሬሽኑ በአዲሱ የበጀት ዓመት የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት ለአገራዊ የቤት ልማት ዕቅድ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል።
ሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር ነው-ተመካካሪዎች
Jul 24, 2026 95
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን በማወያየት ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ውይይት ማድረግ ጀምረዋል። በሀገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙ ወጣቶች ለኢዜአ እንዳሉት፣ የምክክር መድረኩ በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን በምክክር በመፍታት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ወጣት ማርቆስ ገዛኸኝ፤ ከተለያዩ አካባቢዎች ከመጡ ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገር ጉዳይ ለመመካከር ዕድል በማግኘቱ የተሰማውን ደስታ ገልጿል። ሀገራዊ ምክክሩ አንድነትና አብሮነትን በማጎልበት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት እንደሚያስችል ገልጾ፤ ይህም የሀገሪቷን ዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና እንደሚያፋጥን ተናግሯል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ማርታ ተሰማ በበኩሏ፣ በሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ተሳታፊዎች ይበጃል ያሉትን ሃሳብ በነጻነት የሚያንጸባርቁበት መድረክ መፈጠሩን ገልጻለች። ከምክክሩ በኋላም በጠንካራና በሁለንተናዊ መልኩ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት መጓጓቷን ገልጻለች። ሀገራዊ ምክክሩ ወጣቶች የምክክር ባህል እንዲያዳብሩና ለሀገር ዘላቂ ሰላም እና መግባባት ጠቃሚ ሀሳቦችን እንዲያበረክቱ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የተናገረው ደግሞ ወጣት ሮብላሂ አህመድ ነው። ወጣቶች በምክክሩ መሳተፋቸው ከአባቶች ልምድና እውቀት ከመቅሰም ባሻገር ለሀገር መጻኢ ተስፋ የራሳቸውን አሻራ እንዲያኖሩ የሚያስችል ነው ብሏል።
በክልሉ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፍ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት ተከናውነዋል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
Jul 24, 2026 128
አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ እየተካሄደ ባለው የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳመለከቱት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፍ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ከዚህ ውስጥም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ300 ሺህ በላይ ዜጎች በገጠርና በከተማ የስራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። የስራ ዕድል ለተፈጠረላቸው ዜጎችም የመስሪያ እና የመሸጫ ቦታ፣ የመነሻ ካፒታል፣ የገበያ ትስሰር እና የድጋፍና ክትትል ስራዎች መከናወናቸውን ነው የጠቀሱት፡፡   በቱሪዝም ዘርፉም ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ ዘርፉ እየተነቃቃ መምጣቱን ጠቅሰው ክልሉን ከጎበኙ የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎች ከ1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል። በበጀት አመቱ በክልሉ ያለውን የገቢ አማራጮች አሟጦ ለመሰብሰብ በተከናወነው ተግባር 32 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል ነው ያሉት። ከተሞችን ከማልማት አኳያም ለኑሮ ምቹ እና ጽዱ ለማድረግ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንና ከዚህም በ27 ከተሞች እየተገነባ ያለው የኮሪደር ልማት ስራን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ በሌላ በኩል በማህበራዊ ዘርፍም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተው በትምህርትና በጤና የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ከ768 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት በመሰብሰብ የትምህር ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል፣ ግብዓቶችን የማሟላት፣ የመምህራንን አቅም የመገንባትና ሌሎች ስራዎች መከናወናቸውን አመላክተዋል፡፡   በጤናው ዘርፍ የመሰረተ ልማት ግንባታና እና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን እርካታ ማረጋገጥ ያስቻሉ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ የጤና አገልግሎት ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና ያለው የማህበረሰብ ጤና መድህን አባላት ቁጥር እየጨመረ የመጣ ሲሆን ከአንድ ሚሊየን በላይ አባላትን ማፍራት መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ የሚገኝ ሲሆን ምክር ቤት አባላት ርዕሰ መስተዳድሩ ባቀረቧቸው ሪፖርት ዙሪያ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
በቢዝነስ ዲፕሎማሲ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ማስፋትና የቱሪዝም ዘርፉን ከማነቃቃት አኳያ አመርቂ ሥራዎች ተሰርተዋል
Jul 24, 2026 137
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በቢዝነስ ዲፕሎማሲ ማዕቀፍ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ማስፋት፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን መሳብ እና የቱሪዝም ዘርፉን ከማነቃቃት አኳያ አመርቂ ሥራዎች መሰራታቸውን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ ገለጹ። መንግሥት በሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ያሉ ማነቆዎችን በመፍታት ወደ ተሻለ እድገት ጎዳና ለመጓዝ ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ይጠቀሳል። እርምጃውም በሀገር ውስጥ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ የሚሳተፉ የሀገር ውስጥ ኢንቨስተሮችን ከመሳብ ባለፈ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ከመሳብ አኳያ አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን መሳብ የሚያስችል ምቹ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅሞች ያላት ሀገር ናት፡፡ ነገር ግን ይህን ያላትን ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችሉ የአሰራር ስርዓቶችን በመዘርጋት ለሀገር ሁለንተናዊ የልማት እድገት ከማዋል አንጻር ክፍተቶች እንደነበሩ ተናግረዋል። በሀገሪቱ ከዚህ ቀደም የነበሩ የፖሊሲ፣ የሕግና የፋይናንስ ማዕቀፎች ኢትዮጵያ ለውጭ ቀጥታ ኢንቨትመንት ምቹ አለመሆን እንደ ምክንያትነት አንስተዋል። መንግሥት ችግሩን ለመፍታት በወሰዳቸው ሀገር በቀል የማክሮ የኢኮኖሚ ማሻሻያና መዋቅራዊ ለውጦች የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በሀገሪቱ እንዲነቃቃ አቅም ፈጥሯል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ቢዝነስ ምቹ መደላድል መፍጠሯ የውጭ ባለሀብቶችና ድርጅቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ያላቸው ፍላጎት እንዲያድግና የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲጨምር ማድረጉን አስታውቀዋል። ከዚህም ባለፈ ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ምክንያት ከተለመዱት የኢንቨስትመንት ምንጮች በተጨማሪ ከአፍሪካ፣ ከገልፍ እና ከእስያ ሀገራት አዳዲስ ኢንቨስተሮች በስፋት በሀገራችን ኢንቨስት እያደረጉ መሆኑ አንዱ ማሳያ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ለአብነትም በናይጄሪያው ዳንጎቴ ኩባንያ በኩል በሲሚንቶ፣ በማዳበሪያና በሌሎች መስኮች ሰፊ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው የቴሌኮም ዘርፉም ለውጭ ኢንቨስትሮች ክፍት መደረጉን ተከተሎ የኬንያ ኩባንያዎች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን አስታውቀዋል። ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ከሳውዲ አረቢያ፣ ከኩዌት እና ቬይትናም የሚመጡ ባለሀብቶች በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን አንስተው በቬይትናም ኩባንያ የሚከናወነው የሶላር ፓናል ማምረት ስራ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ መሆኑንም አክለዋል። የቢሾፍቱ ኢንተርናሽናል ኤርፖርት ግንባታ መጀመሩ በርካታ ግዙፍ ተቋማት ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት እንዲያሳዩ በር መክፈቱንም አንስተዋል። አምባሳደር ዘሪሁን አያይዘውም መንግሥት የውጭ ቀጥታ ኢንቨትመንትን ለመሳብ የተጀመሩ ስራዎችን ለማስቀጥል ለንፋስ ኃይል፣ ለተፈጥሮ ጋዝ ልማት፣ ለፋርማሲዩቲካል፣ ለግብርና እና ለማምረ ዘርፎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በገበታ ለሀገር ኢንሼቲቭ የተገነቡ የቱሪዝም መሰረተ ልማቶች እንዲሁም በቡና ምርት ላይ የመጡ መዋቅራዊ ለውጦች በርካታ ጎብኚዎችንና ኢንቨስተሮችን እየሳቡ አንደሚገኙ ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን ከሀገር ውጭ ኢንቨስት በማድረግ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ የሚያገኙበት አሰራር መዘርጋቱ ሀገሪቱ ያላትን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድግ መሆኑን አመልክተዋል። ሚኒስቴሩም ከቀደሙት ዋና ዋና ተልዕኮዎቹ መካከል የቢዝነስ ዲፕሎማሲ ግንባር ቀደሙ ነው ብለዋል። ተልዕኮውን እውን ለማድረግም የሀገሪቱን የኢንቨስትመንት እድሎች በማስተዋወቅ፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በመሳብ፣ ለሀገር ውስጥ ምርቶች የውጭ ገበያ በማፈላለግና የቱሪዝም ዘርፉን በማሳደግ በኩል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ድርጅቶችና ግለሰቦች ሀገሪቱን እንዲጎበኙ ከማመቻቸት ጀምሮ፣ ጉብኝቱን ተከታትለው ኢንቨስት እንዲያደርጉ የማነሳሳትና የማግባባት ስራዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሰራ እንደሚገኝ በዚህም ተጨባጭ ለውጦች እየታዩ መሆኑ አመልክተዋል። በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት 4 ነጥብ 32 ቢሊየን ዶላር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ወደ ሀገር ውስጥ መሳብ መቻሉን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 24, 2026 137
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት በከተማዋ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታን በለሚ ኩራ ከፍለ ከተማ ተገኝተው በይፋ አስጀምረዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፥ የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታው ወጣቶችን በክህሎት በማልማት የሀገርን እድገት ለማፋጠን ያለመ ነው ብለዋል። ባለፉት የለውጥ አመታት በመዲናዋ ወጣቶች የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ላይ ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል።   እነዚህ በክህሎትና በቴክኖሎጂ የበቁ ወጣቶች አሁን ላይ ከራሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው አልፈው በሀገር ሁለንተናዊ እድገት ላይ የበኩላቸውን አሻራ እያሳረፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል። አሁን ላይ ወጣቶችን ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ልክ የማብቃት ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። አዲሱ ስማርት ፖሊቴክኒክ የጀርመንን የቴክኒክና ሙያ ልምድ መነሻ በማድረግ፣ በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚገነባና ትውልድ ተሻጋሪ እውቀት የሚገበይበት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኮሌጁ ወጣቶች እውቀትን የሚታጠቁበት፣አዕምሮ እና የሚሰሩ እጆች ተጣጥመው ሀሳብ የሚያፈልቁበት መሆኑን ገልጸዋል። ኮሌጁ በአመት በርካታ አዳዲስ ሰልጣኞችን የመቀበል አቅም እንደሚኖረው ጠቁመው፤ በዘመናዊ ማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሙኒኬሽንና በቴክስታይል ቴክኖሎጂ መስኮች ያሰለጥናል ብለዋል።   ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ፣ በጀትና ጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከተማ አስተዳደሩ በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ በበኩላቸው፤ የሚገነባው ኮሌጅ ወጣቶች በስልጠና ወቅት የሚያመጧቸውን የቴክኖሎጂ ሀሳቦችና የምርምር ውጤቶች ወደ ተግባራዊ ቢዝነስ እንዲቀይሩ፣የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ እንዲመሰርቱና ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችል ነው ብለዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ የመግባባትና የአንድነት ታሪክ እየተጻፈ ነው
Jul 24, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ የመግባባትና የአንድነት ታሪክ እየተጻፈ መሆኑን ዑስታዝ ጀማል በሽር ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ለምክክር የቀረቡ ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በእነዚህ አጀንዳዎች ላይም 4ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ከሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተመካከሩ ይገኛሉ። ዑስታዝ ጀማል ለኢዜአ በሰጡት አስተያየትም፤ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ ታሪክ እየተጻፈበት መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ ቀደም በነበሩ ሥርዓቶች ውሳኔዎች ከላይ ወደ ሕዝብ የሚወርዱበት አሰራር እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ግን ሕዝቦች በመመካከር በጋራ ውሳኔ የሚደርሱበት አውድ ተፈጥሯል ብለዋል። የምክክር ጉባኤም ''ኢትዮጵያ እየመከረች ነው'' የሚለውን መሪ ሃሳብ በሚመጥን መልኩ በሕዝብ ወኪል በሆኑ ተመናካካሪዎች መካከል ግልፅና አሳታፊ ምክክር እየተደረገበት መሆኑን ገልጸዋል። ከሂደቱም የሚጠበቁ ምክረ ሀሳቦች ለኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና ዕድገት የሚያግዙ ውጤቶችን የሚያመጣ መሆኑን ተናግረዋል። በዓለም ላይ በምክክር ችግሮቻቸውን የፈቱ ሀገራት ብዙ ናቸው ያሉት ተመካካሪው፤ የምክክር ጉባኤውም በኢትዮጵያውያን ግልጽ ተሳትፎ መመራቱ ሀገራዊ መግባባትን መፍጠር እንደሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል። ከምክክሩ የሚወጡ ምክረ ሀሳቦች በባለድርሻ አካላት ተግባራዊ ሆነው የሕዝቦችን ተጠቃሚነትና የሀገርን የጋራ ጥቅም የሚያሳድጉ ውጤቶች እንደሚያመጡ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሀሳቦችን ወደ አንድ የጋራ መግባባት ለማምጣት የተከፈተ ታላቅ መድረክ መሆኑንም ተናግረዋል። በምክክር የሚገነባው መግባባትም ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና የጋራ ብልፅግና መሰረት እንደሚሆን አንስተዋል።
የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለችና የጸናች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ትልቅ ዕድል የፈጠረ ነው
Jul 24, 2026 96
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለችና የጸናች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና አራት ሺህ የሕዝብ ተወካይ ተመካካሪዎች በተገኙበት ዋናው የምክክር ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መጀመሩ ይታወቃል።   ከሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮም የክልሎች፣ የከተማ አስተዳደሮችና በውጭ የሚኖሩ ዜጎችን የሚወክሉ ተመካካሪዎች በንዑስ ቡድኖች ተከፋፍለው በተመደቡላቸው አጀንዳዎች ላይ እየተመካከሩ ይገኛሉ። ተመካካሪ ተስፋዬ አየለ እንድገለጹት፤ የምክክር ሂደቱ የጸናች ሀገር ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ ሁነኛ መንገድ በመሆኑ እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የምክክር ጉባኤው ሁሉንም ያካተተ፣ ያሳተፈ እና ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥር ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ለልጆቻችን የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስተላለፍ እየመከሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡   ሊቀ-ካህናት ጌታሰው በላይ በበኩላቸው፤ በምክክሩ የሃይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞች እና ከሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎች በመመካከር ላይ መሆናቸውን አንስተዋል። ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የተፈጠረው ታላቅ ዕድል መሆኑን ጠቅሰው የበለጸገች ሀገርን ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችል ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ይህንን ዕድል በአግባቡ በመጠቀምና አንዱ የአንዱን ሃሳብ በመረዳት ለልጆቻችን የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስተላለፍ እየመከርን ነው ብለዋል።   በምክክሩ ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የሀገርን መጻኢ ዕድል ብሩህ ለማድረግ እየመከሩ መሆናቸውንም የገለጸው ደግሞ ወጣት ቸሩ በየነ ነው። የምክክር ሂደቱ በጥሩ ሁኔታ ተደራጅቶ መጀመሩንና አሁንም በጥሩ ሁኔታ እየሄደ መሆኑን ገልጾ ሁሉንም ያካተተ በመሆኑ ለኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋና ብሩህ መደላድል ይዞ እንደሚመጣ እምነቱን ተናግሯል፡፡   ሌላኛው አስተያያት ሰጪ ማርቆስ ገዛኸኝ ምክክሩ ትስስርን የሚያጠናክር፤ ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋግጥ እንዲሁም መጻኢ ዕድልን የሚወስን በመሆኑ በንቃት አየተሳተፋ መሆኑን ገልጸዋል። ምክክሩ ኢትዮጵያውያን በጋራ የሚቆሙበትን የአንድነት ምዕራፍ ለመፍጠር ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር አመልክተው ሂደቱ ለጠንካራ የሀገር ግንባታ መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር ነው-ተመካካሪዎች
Jul 24, 2026 95
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን በማወያየት ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ውይይት ማድረግ ጀምረዋል። በሀገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙ ወጣቶች ለኢዜአ እንዳሉት፣ የምክክር መድረኩ በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን በምክክር በመፍታት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ወጣት ማርቆስ ገዛኸኝ፤ ከተለያዩ አካባቢዎች ከመጡ ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገር ጉዳይ ለመመካከር ዕድል በማግኘቱ የተሰማውን ደስታ ገልጿል። ሀገራዊ ምክክሩ አንድነትና አብሮነትን በማጎልበት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት እንደሚያስችል ገልጾ፤ ይህም የሀገሪቷን ዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና እንደሚያፋጥን ተናግሯል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ማርታ ተሰማ በበኩሏ፣ በሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ተሳታፊዎች ይበጃል ያሉትን ሃሳብ በነጻነት የሚያንጸባርቁበት መድረክ መፈጠሩን ገልጻለች። ከምክክሩ በኋላም በጠንካራና በሁለንተናዊ መልኩ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት መጓጓቷን ገልጻለች። ሀገራዊ ምክክሩ ወጣቶች የምክክር ባህል እንዲያዳብሩና ለሀገር ዘላቂ ሰላም እና መግባባት ጠቃሚ ሀሳቦችን እንዲያበረክቱ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የተናገረው ደግሞ ወጣት ሮብላሂ አህመድ ነው። ወጣቶች በምክክሩ መሳተፋቸው ከአባቶች ልምድና እውቀት ከመቅሰም ባሻገር ለሀገር መጻኢ ተስፋ የራሳቸውን አሻራ እንዲያኖሩ የሚያስችል ነው ብሏል።
ሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር ነው - ተመካካሪዎች
Jul 24, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ካሉ ኢትዮጵያውያን በማወያየት ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ውይይት ማድረግ ጀምረዋል። በሀገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙ ወጣቶች ለኢዜአ እንዳሉት፣ የምክክር መድረኩ በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን በምክክር በመፍታት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው።   ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ወጣት ማርቆስ ገዛኸኝ፤ ከተለያዩ አካባቢዎች ከመጡ ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገር ጉዳይ ለመመካከር ዕድል በማግኘቱ መደሰቱን ገልጿል። ሀገራዊ ምክክሩ አንድነትና አብሮነትን በማጎልበት ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት እንደሚያስችል ገልጾ፤ ይህም የሀገሪቱን ዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና እንደሚያፋጥን ተናግሯል።   ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ማርታ ተሰማ በበኩሏ፣ በሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ተሳታፊዎች ይበጃል ያሉትን ሃሳብ በነጻነት የሚያንጸባርቁበት መድረክ መፈጠሩን ገልጻለች። ከምክክሩ በኋላም ጠንካራና በሁለንተናዊ መልኩ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት መጓጓቷን ተናግራለች።   ሀገራዊ ምክክሩ ወጣቶች የምክክር ባህል እንዲያዳብሩና ለሀገር ዘላቂ ሰላምና መግባባት ጠቃሚ ሀሳቦችን እንዲያበረክቱ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የተናገረው ደግሞ ወጣት ሮብላሂ አህመድ ነው። ወጣቶች በምክክሩ መሳተፋቸው ከአባቶች ልምድና እውቀት ከመቅስም ባሻገር ለሀገሩ መጻኢ ተስፋ የራሳቸውን አሻራ እንዲያኖሩ የሚያስችል ነው ብሏል።
ሀገራዊ ምክክሩ ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ወደ አንድነት የሚመጡበትን የስምምነት ውል በመፈጸም ጠንካራ ኢትዮጵያን መገንባት የሚያስችል ትልቅ አምድ ነው
Jul 24, 2026 97
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ወደ አንድነት የሚመጡበትን የስምምነት ውል በመፈጸም ጠንካራ ኢትዮጵያን መገንባት የሚያስችል ትልቅ አምድ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት አጀንዳዎች በመለየት ከሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል ዋናውን ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የተጀመረው ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ሂደት በኢትዮጵያውያን መካከል ግልጽ ውይይት በማድረግ ሀገራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን መሰረት የሚጥል ነው፡፡   የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የአለመግባባት ምንጮች በሰለጠነ የሀሳብ ትግል ለመፍታት ምክክር እየተደረገ ነው፡፡ በኢትዮጵየ ለዘመናት እየተንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶች የጋራ ችግሮች በመሆናቸው የችግሮች መፍትሔም የጋራ ድል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የብዝሃ ባህልና ማንነት ህዝቦች መገኛ መሆኗን ገልጸው፤ ታሪካዊው ሀገራዊ ምክክር በህዝቦች መካከል ዘላቂ አብሮነት አንድነትና እኩልነትን ማርጋገጥ ያስችላል ብለዋል፡፡ ሀገራዊ ምክክሩ የበለጸገችና ያደገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትልውድ ለማሸጋገር መሰረት የሚጥሉ ወሳኝ ሀሳቦች የሚመነጩበት መድረክ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ምክክሩ ጠንካራ ሀገረ መንግስት በመመስረት ለባዳና ባንዳ የማትመች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚያስችል ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ የፌደሬሽን ምክር ቤት ለምክክሩ ስኬት ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምስረታ ጀምሮ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን በመግለጽ፤ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት ብለዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክር የጋራ አሸናፊነት ማብሰሪያ፤ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ማሳለጫ ነው-የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች
Jul 23, 2026 367
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክር የጋራ አሸናፊነት ማብሰሪያ፤ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ማሳለጫ መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን በማወያየት ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምክክር ማድረግ ጀምረዋል። በዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪ አቶ አህመድ ሁሴን ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምክክሩ አንዱ የሌላውን ፍላጎት እና አተያይ በአግባቡ እንዲረዳ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነው። ከዚህ ቀደም ሩቅ ሆኖ በአጀንዳዎች ላይ የግል ምልከታን ማንጸባረቅ የተለመደ ነበር ያሉት አመካካሪው፤ አሁን ግን የሌሎችን ስጋት እና ፍላጎት በደንብ ለማየት ልዩ የሆነ እድል መፈጠሩን አንስተዋል። ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ ባህል እና ልምምድ መሆኑን የገለጹት አቶ አህመድ፤ በምክክር ጉባኤው ለሀገር ግንባታ ገንቢና ጠቃሚ ሀሳቦች እየተነሱበት መሆኑን ጠቁመዋል። የምክክር ጉባኤው አሳታፊ እና አካታች መሆኑ የዜጎችን መተማመን እንደሚያሳድገው ጠቅሰው፤ ይህም ለሀገር መንግሥት ግንባታ እንዲሁም ለሀገር ግንባታ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።   ከተመካካሪዎቹ መካከል አቶ መልካሙ ጸጋዬ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም በተቃርኖ ጫፍና ጫፍ ሆነን ስንወጋገዝ ኖረናል ብለዋል።ምክክሩ ለኢትዮጵያ ሁሉም የድርሻውን የሚያበረክትበት አውድ የፈጠረ መሆኑንም ተናግረዋል። በምክክሩ ልማትን ለማፋጠን የሚረዱና የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ሀሳቦች እንደሚፈልቁበት ያላቸውን እምነት ገልጸው፤ ለዚህም እንደ አንድ ተመካካሪ የድርሻዬን ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብለዋል። ምክክር የሁሉ ነገር መፍቻ ቁልፍ በመሆኑ ልዩነትን በኃይል ሳይሆን በምክክር የመፍታት ግብ ይዘን ወደ ምክክሩ መጥተናል ያሉት አቶ መልካሙ፤ የጋራ አሸናፊ የሚያደርገን ይሄው መንገድ ብቻ መሆኑን ገልጸዋለ።   ሌላው ተመካካሪ ወጣት ዮሴፍ አበራ በበኩሉ፤ በምክክሩ ላይ በመሳተፌ ብዙ ልምድ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርጉ ሀሳቦች እየመነጩበት መሆኑን መታዘቡን ገልጿል። ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር ወሳኝ እርምጃ ላይ ነን ያለው ወጣት ዮሴፍ፤ ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርግ ሀሳብ ይዘን ተነስተናል እንደሚሳካም ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ ብሏል።
የሃሳብ መቀራረብን በማጠናከር የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ የሚገነባ ምክክር እያደረግን ነው - የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች
Jul 23, 2026 336
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦ በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ያለምንም ገደብ የሃሳብ መቀራረብንና የጋራ መግባባትን በማጎልበት የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ የሚገነባ ምክክር እያደረጉ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በንዑስ ቡድኖች ተከፋፍለው በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተመካከሩ ነው። የምክክር ጉባኤው ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፣ በኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆዩ ያለመግባባት ጉዳዮችን ለመፍታት በተሰባሰቡ የሕዝብ ወኪሎች እየተካሔደ ያለው ምክክር ለቀጣዩ ትውልድ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ነው። በምክክር ጉባኤው ላይ የሚመከርባቸው አጀንዳዎችም የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ በማጎልበት ሀገራዊ አንድነትን፣ መከባበርንና ዘላቂ መግባባትን የሚያጠናክሩ እንደሆኑም ገልጸዋል። ተመካካሪ ሊቀ ካህናት መልዓከ ሰላም ጌታሰው በላይ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው የሁሉም ዜጎች የሕዝብ ወኪሎች በአንድ መድረክ ተሰባስበው እየመከሩበት የሚገኝ ታሪካዊ ዕድል ነው። ስለ ሀገር አንድነት፣ ሰላምና መግባባት እየመከርን ነው ያሉት ሊቀ ካህናት መልዓከ ሰላም ጌታሰው በላይ፣ በቀጣይም ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት እንዲገነባ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ ፓስተር ጻዲቁ አብዶ በበኩላቸው፣ ምክክር በኃይማኖታዊ አስተምህሮ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው እሴት መሆኑን ጠቅሰዋል። ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤም ለአሁኑና ለመጪው ትውልድ ጠቃሚ ትምህርት የሚያስተላልፍ የኢትጵያዊያን የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ የሐሳብ መሸናነፍ ሳይሆን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የጋራ አሸናፊ ለማድረግ የሚያስችል የመግባባት ሂደት መሆኑንም አመልክተዋል።   ተመካካሪ አባገዳ ደቻሳ ወዳጆ በበኩላቸው፣ ምክክሩ ለትውልድ ተስፋ የሚጣልበት ታሪካዊ የተሞክሮ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ሕዝቡም በተስፋ የሚጠብቀው ሂደት በመሆኑ ስለ ኢትዮጵያ ቀጣይ ዕድገትና ልማት በማሰብ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ በበኩላቸው፣ በምክክሩ የሕዝብ አጀንዳዎችን በነፃነትና በተገቢው መንገድ የሚያቀርቡበት ምቹ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በዚህም በተመረጡት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ጥልቅና ገንቢ ምክክር እያካሄዱ መሆኑን ገልጸዋል። ለሀገራችን ይጠቅማሉ ብለን በምናምንባቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ወደ መግባባት ለመድረስ እየሠራን ነው ብለዋል።   ተመካካሪ አቶ ሳይመን ቶት በበኩላቸው፣ ምክክሩ የመወያየትና የመደማመጥ ባህልን ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፍ ጠንካራ መሠረት በመጣል መግባባት የሰፈነባትን ሀገር ለመገንባት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ፖለቲካ
በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ የመግባባትና የአንድነት ታሪክ እየተጻፈ ነው
Jul 24, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ የመግባባትና የአንድነት ታሪክ እየተጻፈ መሆኑን ዑስታዝ ጀማል በሽር ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ለምክክር የቀረቡ ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በእነዚህ አጀንዳዎች ላይም 4ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ከሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተመካከሩ ይገኛሉ። ዑስታዝ ጀማል ለኢዜአ በሰጡት አስተያየትም፤ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ ታሪክ እየተጻፈበት መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ ቀደም በነበሩ ሥርዓቶች ውሳኔዎች ከላይ ወደ ሕዝብ የሚወርዱበት አሰራር እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ግን ሕዝቦች በመመካከር በጋራ ውሳኔ የሚደርሱበት አውድ ተፈጥሯል ብለዋል። የምክክር ጉባኤም ''ኢትዮጵያ እየመከረች ነው'' የሚለውን መሪ ሃሳብ በሚመጥን መልኩ በሕዝብ ወኪል በሆኑ ተመናካካሪዎች መካከል ግልፅና አሳታፊ ምክክር እየተደረገበት መሆኑን ገልጸዋል። ከሂደቱም የሚጠበቁ ምክረ ሀሳቦች ለኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና ዕድገት የሚያግዙ ውጤቶችን የሚያመጣ መሆኑን ተናግረዋል። በዓለም ላይ በምክክር ችግሮቻቸውን የፈቱ ሀገራት ብዙ ናቸው ያሉት ተመካካሪው፤ የምክክር ጉባኤውም በኢትዮጵያውያን ግልጽ ተሳትፎ መመራቱ ሀገራዊ መግባባትን መፍጠር እንደሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል። ከምክክሩ የሚወጡ ምክረ ሀሳቦች በባለድርሻ አካላት ተግባራዊ ሆነው የሕዝቦችን ተጠቃሚነትና የሀገርን የጋራ ጥቅም የሚያሳድጉ ውጤቶች እንደሚያመጡ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሀሳቦችን ወደ አንድ የጋራ መግባባት ለማምጣት የተከፈተ ታላቅ መድረክ መሆኑንም ተናግረዋል። በምክክር የሚገነባው መግባባትም ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና የጋራ ብልፅግና መሰረት እንደሚሆን አንስተዋል።
የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለችና የጸናች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ትልቅ ዕድል የፈጠረ ነው
Jul 24, 2026 96
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለችና የጸናች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና አራት ሺህ የሕዝብ ተወካይ ተመካካሪዎች በተገኙበት ዋናው የምክክር ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መጀመሩ ይታወቃል።   ከሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮም የክልሎች፣ የከተማ አስተዳደሮችና በውጭ የሚኖሩ ዜጎችን የሚወክሉ ተመካካሪዎች በንዑስ ቡድኖች ተከፋፍለው በተመደቡላቸው አጀንዳዎች ላይ እየተመካከሩ ይገኛሉ። ተመካካሪ ተስፋዬ አየለ እንድገለጹት፤ የምክክር ሂደቱ የጸናች ሀገር ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ ሁነኛ መንገድ በመሆኑ እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የምክክር ጉባኤው ሁሉንም ያካተተ፣ ያሳተፈ እና ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥር ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ለልጆቻችን የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስተላለፍ እየመከሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡   ሊቀ-ካህናት ጌታሰው በላይ በበኩላቸው፤ በምክክሩ የሃይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞች እና ከሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎች በመመካከር ላይ መሆናቸውን አንስተዋል። ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የተፈጠረው ታላቅ ዕድል መሆኑን ጠቅሰው የበለጸገች ሀገርን ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችል ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ይህንን ዕድል በአግባቡ በመጠቀምና አንዱ የአንዱን ሃሳብ በመረዳት ለልጆቻችን የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስተላለፍ እየመከርን ነው ብለዋል።   በምክክሩ ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የሀገርን መጻኢ ዕድል ብሩህ ለማድረግ እየመከሩ መሆናቸውንም የገለጸው ደግሞ ወጣት ቸሩ በየነ ነው። የምክክር ሂደቱ በጥሩ ሁኔታ ተደራጅቶ መጀመሩንና አሁንም በጥሩ ሁኔታ እየሄደ መሆኑን ገልጾ ሁሉንም ያካተተ በመሆኑ ለኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋና ብሩህ መደላድል ይዞ እንደሚመጣ እምነቱን ተናግሯል፡፡   ሌላኛው አስተያያት ሰጪ ማርቆስ ገዛኸኝ ምክክሩ ትስስርን የሚያጠናክር፤ ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋግጥ እንዲሁም መጻኢ ዕድልን የሚወስን በመሆኑ በንቃት አየተሳተፋ መሆኑን ገልጸዋል። ምክክሩ ኢትዮጵያውያን በጋራ የሚቆሙበትን የአንድነት ምዕራፍ ለመፍጠር ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር አመልክተው ሂደቱ ለጠንካራ የሀገር ግንባታ መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር ነው-ተመካካሪዎች
Jul 24, 2026 95
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን በማወያየት ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ውይይት ማድረግ ጀምረዋል። በሀገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙ ወጣቶች ለኢዜአ እንዳሉት፣ የምክክር መድረኩ በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን በምክክር በመፍታት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ወጣት ማርቆስ ገዛኸኝ፤ ከተለያዩ አካባቢዎች ከመጡ ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገር ጉዳይ ለመመካከር ዕድል በማግኘቱ የተሰማውን ደስታ ገልጿል። ሀገራዊ ምክክሩ አንድነትና አብሮነትን በማጎልበት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት እንደሚያስችል ገልጾ፤ ይህም የሀገሪቷን ዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና እንደሚያፋጥን ተናግሯል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ማርታ ተሰማ በበኩሏ፣ በሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ተሳታፊዎች ይበጃል ያሉትን ሃሳብ በነጻነት የሚያንጸባርቁበት መድረክ መፈጠሩን ገልጻለች። ከምክክሩ በኋላም በጠንካራና በሁለንተናዊ መልኩ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት መጓጓቷን ገልጻለች። ሀገራዊ ምክክሩ ወጣቶች የምክክር ባህል እንዲያዳብሩና ለሀገር ዘላቂ ሰላም እና መግባባት ጠቃሚ ሀሳቦችን እንዲያበረክቱ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የተናገረው ደግሞ ወጣት ሮብላሂ አህመድ ነው። ወጣቶች በምክክሩ መሳተፋቸው ከአባቶች ልምድና እውቀት ከመቅሰም ባሻገር ለሀገር መጻኢ ተስፋ የራሳቸውን አሻራ እንዲያኖሩ የሚያስችል ነው ብሏል።
ሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር ነው - ተመካካሪዎች
Jul 24, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ካሉ ኢትዮጵያውያን በማወያየት ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ውይይት ማድረግ ጀምረዋል። በሀገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙ ወጣቶች ለኢዜአ እንዳሉት፣ የምክክር መድረኩ በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን በምክክር በመፍታት ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው።   ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ወጣት ማርቆስ ገዛኸኝ፤ ከተለያዩ አካባቢዎች ከመጡ ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገር ጉዳይ ለመመካከር ዕድል በማግኘቱ መደሰቱን ገልጿል። ሀገራዊ ምክክሩ አንድነትና አብሮነትን በማጎልበት ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት እንደሚያስችል ገልጾ፤ ይህም የሀገሪቱን ዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና እንደሚያፋጥን ተናግሯል።   ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ማርታ ተሰማ በበኩሏ፣ በሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ተሳታፊዎች ይበጃል ያሉትን ሃሳብ በነጻነት የሚያንጸባርቁበት መድረክ መፈጠሩን ገልጻለች። ከምክክሩ በኋላም ጠንካራና በሁለንተናዊ መልኩ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት መጓጓቷን ተናግራለች።   ሀገራዊ ምክክሩ ወጣቶች የምክክር ባህል እንዲያዳብሩና ለሀገር ዘላቂ ሰላምና መግባባት ጠቃሚ ሀሳቦችን እንዲያበረክቱ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የተናገረው ደግሞ ወጣት ሮብላሂ አህመድ ነው። ወጣቶች በምክክሩ መሳተፋቸው ከአባቶች ልምድና እውቀት ከመቅስም ባሻገር ለሀገሩ መጻኢ ተስፋ የራሳቸውን አሻራ እንዲያኖሩ የሚያስችል ነው ብሏል።
ሀገራዊ ምክክሩ ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ወደ አንድነት የሚመጡበትን የስምምነት ውል በመፈጸም ጠንካራ ኢትዮጵያን መገንባት የሚያስችል ትልቅ አምድ ነው
Jul 24, 2026 97
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ወደ አንድነት የሚመጡበትን የስምምነት ውል በመፈጸም ጠንካራ ኢትዮጵያን መገንባት የሚያስችል ትልቅ አምድ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት አጀንዳዎች በመለየት ከሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል ዋናውን ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የተጀመረው ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ሂደት በኢትዮጵያውያን መካከል ግልጽ ውይይት በማድረግ ሀገራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን መሰረት የሚጥል ነው፡፡   የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የአለመግባባት ምንጮች በሰለጠነ የሀሳብ ትግል ለመፍታት ምክክር እየተደረገ ነው፡፡ በኢትዮጵየ ለዘመናት እየተንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶች የጋራ ችግሮች በመሆናቸው የችግሮች መፍትሔም የጋራ ድል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የብዝሃ ባህልና ማንነት ህዝቦች መገኛ መሆኗን ገልጸው፤ ታሪካዊው ሀገራዊ ምክክር በህዝቦች መካከል ዘላቂ አብሮነት አንድነትና እኩልነትን ማርጋገጥ ያስችላል ብለዋል፡፡ ሀገራዊ ምክክሩ የበለጸገችና ያደገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትልውድ ለማሸጋገር መሰረት የሚጥሉ ወሳኝ ሀሳቦች የሚመነጩበት መድረክ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ምክክሩ ጠንካራ ሀገረ መንግስት በመመስረት ለባዳና ባንዳ የማትመች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚያስችል ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ የፌደሬሽን ምክር ቤት ለምክክሩ ስኬት ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምስረታ ጀምሮ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን በመግለጽ፤ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት ብለዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክር የጋራ አሸናፊነት ማብሰሪያ፤ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ማሳለጫ ነው-የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች
Jul 23, 2026 367
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክር የጋራ አሸናፊነት ማብሰሪያ፤ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ማሳለጫ መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን በማወያየት ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምክክር ማድረግ ጀምረዋል። በዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪ አቶ አህመድ ሁሴን ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምክክሩ አንዱ የሌላውን ፍላጎት እና አተያይ በአግባቡ እንዲረዳ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነው። ከዚህ ቀደም ሩቅ ሆኖ በአጀንዳዎች ላይ የግል ምልከታን ማንጸባረቅ የተለመደ ነበር ያሉት አመካካሪው፤ አሁን ግን የሌሎችን ስጋት እና ፍላጎት በደንብ ለማየት ልዩ የሆነ እድል መፈጠሩን አንስተዋል። ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ ባህል እና ልምምድ መሆኑን የገለጹት አቶ አህመድ፤ በምክክር ጉባኤው ለሀገር ግንባታ ገንቢና ጠቃሚ ሀሳቦች እየተነሱበት መሆኑን ጠቁመዋል። የምክክር ጉባኤው አሳታፊ እና አካታች መሆኑ የዜጎችን መተማመን እንደሚያሳድገው ጠቅሰው፤ ይህም ለሀገር መንግሥት ግንባታ እንዲሁም ለሀገር ግንባታ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።   ከተመካካሪዎቹ መካከል አቶ መልካሙ ጸጋዬ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም በተቃርኖ ጫፍና ጫፍ ሆነን ስንወጋገዝ ኖረናል ብለዋል።ምክክሩ ለኢትዮጵያ ሁሉም የድርሻውን የሚያበረክትበት አውድ የፈጠረ መሆኑንም ተናግረዋል። በምክክሩ ልማትን ለማፋጠን የሚረዱና የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ሀሳቦች እንደሚፈልቁበት ያላቸውን እምነት ገልጸው፤ ለዚህም እንደ አንድ ተመካካሪ የድርሻዬን ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብለዋል። ምክክር የሁሉ ነገር መፍቻ ቁልፍ በመሆኑ ልዩነትን በኃይል ሳይሆን በምክክር የመፍታት ግብ ይዘን ወደ ምክክሩ መጥተናል ያሉት አቶ መልካሙ፤ የጋራ አሸናፊ የሚያደርገን ይሄው መንገድ ብቻ መሆኑን ገልጸዋለ።   ሌላው ተመካካሪ ወጣት ዮሴፍ አበራ በበኩሉ፤ በምክክሩ ላይ በመሳተፌ ብዙ ልምድ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርጉ ሀሳቦች እየመነጩበት መሆኑን መታዘቡን ገልጿል። ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር ወሳኝ እርምጃ ላይ ነን ያለው ወጣት ዮሴፍ፤ ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርግ ሀሳብ ይዘን ተነስተናል እንደሚሳካም ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ ብሏል።
የሃሳብ መቀራረብን በማጠናከር የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ የሚገነባ ምክክር እያደረግን ነው - የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች
Jul 23, 2026 336
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦ በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ያለምንም ገደብ የሃሳብ መቀራረብንና የጋራ መግባባትን በማጎልበት የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ የሚገነባ ምክክር እያደረጉ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በንዑስ ቡድኖች ተከፋፍለው በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተመካከሩ ነው። የምክክር ጉባኤው ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፣ በኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆዩ ያለመግባባት ጉዳዮችን ለመፍታት በተሰባሰቡ የሕዝብ ወኪሎች እየተካሔደ ያለው ምክክር ለቀጣዩ ትውልድ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ነው። በምክክር ጉባኤው ላይ የሚመከርባቸው አጀንዳዎችም የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ በማጎልበት ሀገራዊ አንድነትን፣ መከባበርንና ዘላቂ መግባባትን የሚያጠናክሩ እንደሆኑም ገልጸዋል። ተመካካሪ ሊቀ ካህናት መልዓከ ሰላም ጌታሰው በላይ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው የሁሉም ዜጎች የሕዝብ ወኪሎች በአንድ መድረክ ተሰባስበው እየመከሩበት የሚገኝ ታሪካዊ ዕድል ነው። ስለ ሀገር አንድነት፣ ሰላምና መግባባት እየመከርን ነው ያሉት ሊቀ ካህናት መልዓከ ሰላም ጌታሰው በላይ፣ በቀጣይም ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት እንዲገነባ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ ፓስተር ጻዲቁ አብዶ በበኩላቸው፣ ምክክር በኃይማኖታዊ አስተምህሮ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው እሴት መሆኑን ጠቅሰዋል። ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤም ለአሁኑና ለመጪው ትውልድ ጠቃሚ ትምህርት የሚያስተላልፍ የኢትጵያዊያን የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ የሐሳብ መሸናነፍ ሳይሆን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የጋራ አሸናፊ ለማድረግ የሚያስችል የመግባባት ሂደት መሆኑንም አመልክተዋል።   ተመካካሪ አባገዳ ደቻሳ ወዳጆ በበኩላቸው፣ ምክክሩ ለትውልድ ተስፋ የሚጣልበት ታሪካዊ የተሞክሮ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ሕዝቡም በተስፋ የሚጠብቀው ሂደት በመሆኑ ስለ ኢትዮጵያ ቀጣይ ዕድገትና ልማት በማሰብ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል።   ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ በበኩላቸው፣ በምክክሩ የሕዝብ አጀንዳዎችን በነፃነትና በተገቢው መንገድ የሚያቀርቡበት ምቹ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በዚህም በተመረጡት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ጥልቅና ገንቢ ምክክር እያካሄዱ መሆኑን ገልጸዋል። ለሀገራችን ይጠቅማሉ ብለን በምናምንባቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ወደ መግባባት ለመድረስ እየሠራን ነው ብለዋል።   ተመካካሪ አቶ ሳይመን ቶት በበኩላቸው፣ ምክክሩ የመወያየትና የመደማመጥ ባህልን ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፍ ጠንካራ መሠረት በመጣል መግባባት የሰፈነባትን ሀገር ለመገንባት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ማህበራዊ
የድሬዳዋ አስተዳደር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ተግባራትን እያከናወነ ነው
Jul 24, 2026 63
ድሬደዋ፣ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦የድሬዳዋ አስተዳደር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህን ጨምሮ የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና ነዋሪዎች ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ንግስ በአል ድሬዳዋ ለመጡ ምዕመናንና እንግዶች አቀባበል አድርገዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በወቅቱ እንዳሉት፥ ከተማዋ በህብረ ብሔራዊ አንድነት የደመቀች በመሆኗ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለሚያጠናክሩ ተግባራት ትኩረት በመስጠት እየተከናወኑ ነው። ድሬዳዋ እንግዶችን በፍቅር የመቀበል ልምድ ያላት መሆኗም የዚሁ መገለጫ መሆኑን ጠቁመው የዛሬው አቀባበልም ይህንኑ በተግባር ያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማዋ የሰላም፣ የልማትና የፍቅር ተምሳሌት በመሆኗም ለኃይማኖታዊም ሆነ ሌሎች ሁነቶች ተመራጭነቷ እያደገ መምጣቱን አመልክተዋል። ድሬዳዋ የዜጎች የርስ በርስ ትስስር ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት መጠናከር መሰረት መሆኑን በተግባር አሳይታለች ያሉት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ በበኩላቸው መምሪያው የቁሉቢ ገብርኤል አመታዊ ንግስ በአል ታዳሚዎች በድሬዳዋ ቆይታቸው ሰላማዊ ጊዜ እንዲያሳልፉ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። ለኃይማኖታዊ ክብረ በአሉ ወደ ድሬዳዋ ከመጡ ምዕመናን መካከል አቶ ስዩም ታደሰ እና አቶ የፈቃዱ አስናቀ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና ነዋሪዎች ያደረጉላቸው አቀባበልና መስተንግዶ አስደስቷቸዋል።
በክልሉ እየተከናወነ ያለው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለተቸገሩ ወገኖች አለኝታና የመረዳዳት እሴት እንዲጠናከር እያደረገ ነው
Jul 24, 2026 90
ሆሳዕና፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እየተከናወነ ያለው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለተቸገሩ ወገኖች አለኝታ ከመሆን ባለፈ የመረዳዳት እሴት እንዲጠናከር እያደረገ መሆኑን የክልሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን በሆሳዕና ከተማ ለስድስት አቅመ ደካሞች የመኖሪያ ቤት ግንባታና ለ1 ሺህ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ የማሰባሰብ ሥራ አስጀምሯል።   በመርሐ ግብሩ የተገኙት ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለተቸገሩ ወገኖች አለኝታ ከመሆን ባለፈ የመረዳዳት እሴት እንዲጠናከር እያደረገ ይገኛል። በተያዘው ክረምትም አገልግሎቱን በማስቀጠል በርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ የመንግሥት ወጪ እንዲቀንስ አስችሏል ብለዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱን ለማሳካት ከአጋር አካላት ጋር ሲሠራ መቆየቱን አንስተው፣ በሆሳዕና ከተማ ለአቅመ ደካሞች ቤት ለመገንባት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ያስጀመረው ሥራም የተጀመረው ጥረት አካል መሆኑን ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ባለሥልጣኑ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሆሳዕና ከተማ ለስድስት አቅመ ደካሞች የመኖሪያ ቤቶችን የመገንባትና ለ1 ሺህ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ የማሰባሰብ ሥራ መጀመሩን ጠቅሰዋል።   የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሳሙኤል ሽጉጤ በበኩላቸው፣ በከተማው በ16 የተለያዩ ዘርፎች ከ2 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል። የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ሠራተኞች በከተማው በአገልግሎቱ ለመሳተፍ ያሳዩት ቁርጠኝነት በከተማው የተጀመረውን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ ለማጠናከር አጋዥ ስለመሆኑም ገልጸዋል።
ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ ቅርሶችን በመጠበቅ ለሀብት ምንጭነት ለማዋል እየተሰራ ነው
Jul 24, 2026 97
ጎንደር፤ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ጥንታዊ ቅርሶችን በመጠገን፣ በማደስና በዘመናዊ ሥርዓት በመያዝ የሃብት ምንጭ ሆነው እንዲቀጥሉ እየተሰራ ያለው ስራ ውጤታማ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ገለጹ። የባለስልጣኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በጎንደር ከተማ የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ​ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ነባር ቅርሶችን በማደስና አዳዲስ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የሀብት ምንጭ የማድረግ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቷቸዋል። በዚህም ቅርሶችን በመጠበቅ፣ በመንከባከብና በማደስ የኢኮኖሚ ምንጭ የማድረግ ፍልስፍናው በተሳካ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   የጎንደር አብያተ መንግስታትን፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የጅማ አባጅፋር ቤተ መንግስትን፣ የሐረር ቅርሶችንና የነቀምት የቁምሳ ሞረዳ ቤተመንግስት እድሳት ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ​በዋና ዋና የቅርስ መገኛ አካባቢዎች ሙዚየሞችን በማስገንባት እና ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን ለጎብኝዎች ክፍት በማድረግ የሀብት ምንጭ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። የአዝማሪ ጨዋታዎችን ጨምሮ የሀገር ባህል ዘፈኖችና ጭፈራዎችን ወደ አደባባይ በማውጣት የገጠሩን ቱሪዝ ልማት በማሳደግ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የጎንደር ከተማ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ማርያም ካሳሁን እንደገለጹት፣ በከተማዋ የተከናወነው የኮሪደር ልማትና የታሪካዊ አብያተ መንግስታት እድሳት የቱሪዝሙ ዘርፉን እንዲነቃቃ አድርጓል። በዚህም በ2017 በጀት ዓመት አንድ ሺህ 914 የነበረው የውጭ ሀገር ቱሪስቶች ቁጥር በ2018 በጀት ዓመት ወደ ስድስት ሺህ 420 ማደግ መቻሉን በማሳያነት አቅርበዋል። ባለስልጣኑም በጎንደር ከተማ ለሚገኘው የደብረ ብርሃን ሥላሴ ጥገና በመጀመሪያው ምእራፍ 30 ሚሊዮን ብር መመደቡን ጠቁመው ሌሎች ቅርሶችንም ደረጃ በደረጃ እንደሚታደሱ ነው የተናገሩት። ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹ በቅርቡ የታደሰው የፋሲል አብያተ መንግስትን ጨምሮ ሌሎች በከተማዋ የሚገኙ የመስህብ ህብቶችን ጎብኝተዋል።
የበጎ ፈቃድ ነጻ የሕክምና አገልግሎት የጤና አገልግሎትን ለሁሉም ማህበረሰብ ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ ጤናማ ዜጋ ለመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው
Jul 24, 2026 157
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የበጎ ፈቃድ ነጻ የሕክምና አገልግሎት የጤና አገልግሎትን ለሁሉም ማህበረሰብ ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ ብቁና ጤናማ ዜጋ ለመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ፡፡ «በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ» በሚል መሪ ሐሳብ የጤና ሚኒስቴር ከቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በጋራ ያዘጋጀው የክረምት የበጎ ፈቃድ የነፃ የጤና ምርመራ፣ ምክርና ሕክምና አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በጉለሌ ክፍለ ከተማ በይፋ ተጀምሯል።   መርሃ ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወነው የክረምት የበጎ ፈቃድ ሕክምና አገልግሎት ዋና ዓላማ በሽታዎችን ቀድሞ መከላከልና መለየት ላይ ያተኮረ ነው። ይህ አገልግሎት ዜጎች ቀድመው ሕክምና የሚያገኙበት ትልቅ ዕድል መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ዶክተር አብረሃም እሸቴ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በየዓመቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንደሚያካሂድ ጠቁመዋል። በዘንድሮው የክረምት መርሃ ግብርም ከ120ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተለያዩ ነፃ የሕክምና አገልግሎቶችን ለማቅረብ መታቀዱን ገልጸዋል።   አገልግሎቱም ከተለመዱት መደበኛ ምርመራዎች ባሻገር የቀዶ ሕክምና፣ የስፔሻሊቲ ሕክምናዎች እንዲሁም እንደ ሲቲ ስካን (CT Scan) እና ኤም አር አይ (MRI) ያሉ የላቁ የዲያግኖስቲክ ምርመራዎችን ያካተተ መሆኑን አስረድተዋል። የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ከሕክምና ሥራዎች ጎን ለጎን በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን መተከል፣ የአቅመ ደካሞች ቤቶችን ማደስ፣ ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግና የማዕድ ማጋራትን እንደሚያካተት ተጠቅሷል፡፡  
ኢኮኖሚ
በሲዳማ ክልል በበልግ እርሻ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት ተከናውነዋል - ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Jul 24, 2026 36
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በበልግ ወቅት እርሻ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳደሩን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች በሀዋሳ ዙሪያ፣ በደራራ፣ በብላቴ ዙሪያ እና በዳሌ ወረዳዎች በበልግ የለማ ማሳ የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንዳሉት በልግ አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች በበቆሎ፣ ቦሎቄና ሌሎች ሰብሎች የለማው ማሳ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል።   በምርት ወቅቱ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለግብአት አጠቃቀምና ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት ተሰጥቶ መከናወኑን ጠቁመዋል። በበልግ እርሻው ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት በመኽር ወቅትም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።   የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ ታምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ በበልግ እርሻ 152 ሺህ ሄክታር ማሳ በበቆሎ፣ ቦሎቄና ስራ ስር ሰብሎች መልማቱን ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥ 67 ሺህ ሄክታር የሚሆነው በበቆሎ መልማቱን ጠቁመው በምርት የተሸፈነውን ማሳ ውጤታማ ለማድረግም የእንክብካቤና የክትትል ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አመልክተዋል፡፡   የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አለማየሁ ዲጋ በበኩላቸው አንድ ሄክታር ማሳ ላይ ያለሙት በቆሎ በመልካም ቁመና ላይ መሆኑን ተናግረዋል። ከግብርና ባለሙያ በሚሰጣቸው ምክር በመታገዝ እርጥበትን በማሳ ውስጥ እንዲቆይ በማድረጋቸው የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ አመላክተዋል።   አርሶ አደር ጸሀይ በቀለ በበኩላቸው በማሳቸው ውስጥ እርጥበትን የማቆየት ስራ በመስራታቸው የበቆሎ ሰብላቸው በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ኮርፖሬሽኑ ያደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ለተከታታይ ዓመታት በውጤታማነት እንዲቀጥል አስችሎታል
Jul 24, 2026 43
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጡን መነሻ ያደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ለተከታታይ ዓመታት ውጤታማነቱ እንዲረጋገጥ እንዳስቻለው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ገለፀ። የኮርፖሬሽኑ በ2019 በጀት ዓመትም ይህንኑ አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ስትራቴጂካዊ አቅጣጫም ተቀምጧል። ኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ውይይቱን አካሂዷል። በዚህ የግምገማ መድረክ በበጀት ዓመቱ የተቀመጠውን ዕቅድ 97 በመቶ ማከናወን መቻሉ የተገለፀ ሲሆን፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በገቢ ዕድገት፣ በቤት ልማት፣ በመስፈጸም አቅም እና በቤት አስተዳደር ረገድ የተከናወኑት ሥራዎች የተቋሙን አጠቃላይ የለውጥ ጉዞ ማረጋገጣቸው ተጠቁሟል።   በተጨማሪም የሕዝብና የመንግስት ጥቅም ለማስጠበቅ በፍርድ ቤት በተከናወኑ ክርክሮች በርካታ ይዞታዎችን ማስመለስ ተችሏል ብሏል። ኮርፖሬሽኑ በምሥራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ገበያ ለመሰማራት ያስቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት፣ በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ልማት ለመሳተፍ ከደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያል ስቴት ጋር የተደረሰው ስምምነት ወደ ተግባር ለማስገባት ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ አስታውቋል። የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ የፒያሳ እና የጎልድ ሳይት ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ አገልግሎት ማስገባት የተቻለ ሲሆን፣ ዘመናዊ የ3ዲ የግንባታ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት የሚያስችሉ የመጀመሪያዎቹ የሙከራ ቤቶች ግንባታም በመከናወን ላይ ይገኛሉ። በሌላ በኩል የቤቶች ቆጠራና የመረጃ ማሰባሰብ ሥራ በመጠናቀቁ ዘመናዊ የቤት አስተዳደር ሥርዓትን ማጠናከር የተቻለ ሲሆን፣ በርካታ የንግድ ቤቶችም ከደንበኞች ጋር በትብብር ተገንብተው ወደ ኪራይ አገልግሎት በመግባታቸው ከፍተኛ ገቢ ማስገኘት ጀምረዋል። ከዚህ ባሻገር የተቋሙን የ50 ዓመት የጉዞ ታሪክና ስኬቶች የሚያስተዋውቁ የተለያዩ መርሐግብሮች በኢዮቤልዩ በዓሉ ወቅት ለአራት ተከታታይ ቀናት በታላቅ ድምቀት ተከብረዋል። በዚህም የተቋሙን ገጽታ መቀየር መቻሉም ነው የተገለጸው፡፡ በአዲሱ የ2019 በጀት ዓመት ዘመናዊና ፈጣን የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ሥራ ላይ ማዋል፣ የሀገር ውስጥ የቤት አቅርቦትን ለማሳደግ ሰፋፊ የቤት ልማት መርሐግብሮችን መተግበር፣ አዳዲስ አሰራሮችን በመጠቀም የገቢ ምንጮችንና የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋፋት እንዲሁም የሰው ኃይል እና የአሰራር ሥርዓት አቅምን ማጠናከር ዋነኛ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ሆነው ተቀምጠዋል። ኮርፖሬሽኑ በአዲሱ የበጀት ዓመት የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት ለአገራዊ የቤት ልማት ዕቅድ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል።
በሀረሪ ክልል በበጀት ዓመቱ 6 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል
Jul 24, 2026 79
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል ገቢዎች ቢሮ በተያዘው በጀት ዓመት 6 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አስታወቀ። በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማትና የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች ለመመለስ ትኩረት መሰጠቱም ተመላክቷል። የቢሮ ኃላፊው ያሲን አብዱላሂ እንደገለጹት በ2019 በጀት ዓመት የግብር ዘመን 6 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከሐምሌ 1/2018 ጀምሮ ሥራው መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት የገቢ አሰባሰብ ሥራው በቴክኖሎጂ መታገዙ፣ የባለሙያዎች አቅም መገንባቱና የገቢ ምንጮችን ማስፋት በመቻሉ ገቢን ማሳደግ ተችሏልም ነው ያሉት፡፡ በተያዘው የግብር ዘመንም የተጨማሪ እሴት ታክስ ገቢን የማሳደግ፣ ከቅጥር የሚገኝ ገቢን እና የአከራይ ተከራይ ገቢን አሟጦ የመሰብሰብ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል፡፡ በክልሉ ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ ከጥሬ ገንዘብ ንክኪ ነፃ የሆነ የገቢ አሰባሰብ ሥርዐት በመዘርጋት በባንክ የክፍያ ማረጋገጫ ብቻ ገቢ እየተሰበሰበ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማትና የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች ለመመለስ ትኩረት መሰጠቱንም አመልክተዋል። ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ ባለው የገቢ አሰባሰብ ሂደት ግብር ከፋዮች ግብራቸውን እየከፈሉ እንደሚገኙም አቶ ያሲን ጠቁመዋል፡፡ ደንበኛ ተኮር አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው ሊፈጠር የሚችለውን ጫና ለመቀነስና ለግብር ከፋዩ አማራጭ የአገልግሎት ጊዜ ለመስጠት ሲባልም በዚህ የግብር ወቅት በተወሰኑ ሠራተኞች እስከ ምሽቱ 2 ሰአት ድረስ አገልግሎት የሚሠጥ መሆኑን ገልፀዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀማችን ወጪን ከመቀነስ ባለፈ ምርታማነታችን እያሳደገልን ነው - አርሶ አደሮች
Jul 24, 2026 87
መቱ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በኢሉባቦር ዞን በቀያቸው አዘጋጅተው እየተጠቀሙ ያሉት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ወጪ ከመቀነስ ባለፈ ምርታማነታቸውን እያሳደገ መሆኑን የዞኑ አርሶ አደሮች ገለጹ።   በኢሉአባቦር ዞን በበቾ ወረዳ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በማምረት እየተጠቀሙ ካሉት አርሶ አደሮች መካከል ወይዘሮ አይናለም ጌታቸው አንዷ ናቸው። ወይዘሮ አይናለም እንዳሉት፣ በግብርና ባለሙያዎች እገዛ ከአካባቢያቸው በሚገኙ ተረፈ ምርቶችና ዕፅዋት የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት መጠቀማቸው ከዚህ በፊት ለዘመናዊ ማዳበሪያ ይወጣ የነበረውን ወጪ ከማስቀረቱ በላይ የምርት መጠንን ማሳደጉን ገልጸዋል።   የዲዱ ወረዳ አርሶ አደሩ ገዳሙ አርፋሳ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በማዘጋጀት ለእርሻ ሥራቸው እየተጠቀሙ መሆኑንና ከራሳቸው ፍጆታ አልፈው ለሌሎች በመሸጥ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ እንደሆናቸው ተናግረዋል። የተፈጥሮ ማዳበሪያው የመሬት ለምነትን ጠብቆ የሚያቆይ በመሆኑ፣ ምርታማነት ለዓመታት ቀጣይነት እንዲኖረው ያስችላል ብለዋል።   በበቾ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተስፋዬ ዲቤሳ እንደተናገሩት በወረዳው የምርትና ምርታማነት ዕድገትን ለማረጋገጥ አርሶ አደሮቹን ተጠቃሚ ለማድረግ በተፈጥሮ ማዳበሪያ ዙሪያ በተሠራው ሥራ ውጤት እየመጣ ነው።   የኢሉአባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ዳኜ ፍቅሬ እንደገለጹት በዞኑ በምርት ዘመኑ ከ265 ሺህ ኩንታል በላይ ዘመናዊ ማዳበሪያና ከ11 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው። በዚህም የዞኑ አርሶ አደር ባለው መሬት ላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘጋጅቶ በመጠቀም ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን አንስተው፣ ልምድም እያዳበሩ ነው ብለዋል። በወረዳዎቹ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጃ ማዕከላት ተገንብተው ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቁመው ለአርሶ አደሮች እንዲደርስ መደረጉን ገልጸዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በክልሉ የግብር አከፋፈል ስርአቱን ቀልጣፋና አስተማማኝ ለማድረግ እየተሰራ ነው
Jul 24, 2026 35
ባህርዳር፤ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የግብር አከፋፈል ስርአቱን በቴሌ ብር በማድረግ ቀልጣፋና አስተማማኝ ስርአት ለመዘርጋት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የግብር አከፋፈል ስርአቱን በቴሌ ብር ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ኢትዮ ቴሌኮም ጋር ዛሬ ማምሻውን ተፈራርሟል። የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ /ር) በወቅቱ እንደገለጹት፥ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ90 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ በራስ አቅም የመልማት ባህልን በማጎልበት አበረታች ውጤት ተገኝቷል። በአዲሱ በጀት ዓመትም የግብር ስርአቱን ዲጅታላይዝ በማድረግ ግልጽ፣ ቀልጣፋና ተአማኒነት ያለው የግብር ስርአት ለመገንባት ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲና ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የተደረሰው ስምምነትም ወደ ኢ-ታክስ ሲስተም የገቡ 420 ሺህ የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮችን ጨምሮ የደረጃ "ሀ" እና "ሐ" ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በቀላሉና በፍጥነት ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲከፍሉ የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪም የግብር ስርአቱን ተደራሽ ለማድረግና በዘርፉ የሚስተዋለውን ብልሹ አሰራር ለማስቀረት የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ችፍ የሞባይል ባንኪንግ ቢዝነስ ኦፊሰር አቶ ቡሩክ አዳነ በበኩላቸው፥ ከክልሉ ገቢዎች ቢሮ ጋር የተደረገው ስምምነት ዲጅታል 2030ን እውን ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል። ቢሮው ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ያበለጸገውን የኢ-ታክስ ሲስተም ከቴሌ ብር ጋር በማስተሳሰር ደንበኞች በቀላሉ ግብራቸውን የሚከፍሉበት ስርአት ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የግብር ክፍያውን በቴሌ ብር ለማድረግም በዩኒቨርሲቲው የበለጸገውን ሲስተም ከቴሌብር ጋር እንዲናበብ በማድረግ፣አሰራሩን በመፈተሽና የደህንነት ጉዳዮችን የማረጋገጥ ስራ ቀድሞ ማጠናቀቁን ተናግረዋል። ደንበኞችም ከገቢዎች ቢሮ የሚሰጠውን የመክፈያ ኮድ በማስገባት ግብራቸውን በቴሌብር በቀላሉ፣ በፍጥነትና አስተማማኝነት ባለው መንገድ እንዲከፍሉ የሚያስችል ነው ብለዋል። አያይዘውም ኩባንያው ቴሌብር የሚጠቀሙ ደንበኞችን ቁጥር 60 ነጥብ 5 ሚሊየን ማድረሱን ጠቁመው ባለፉት አምስት ዓመታትም 9 ትሪሊዮን የሚጠጋ የገንዘብ ዝውውር ማድረግ መቻሉን አውስተዋል። የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር፣ ምርምር፣ ማህብረሰብ አገልግሎትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ባሻገር ከተቋማት ጋር በቅንጅት ለሀገር እድገት የሚበጁ ተግባራትን አያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ከክልሉ ገቢዎች ቢሮ ጋር በመተባበርም የኢ-ታክስ ፕሮጀክትን በማልማት የዘርፉን ችግር ለመፍታት መስራቱን ጠቁመው፥ አሁን ላይ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የተደረሰው ስምምነት የኢ-ታክስ ሲስተሙን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ነው ሲሉ አክለዋል። ማምሻውን በተካሄደው ስምምነት ላይም የቢሮው የማኔጅመንት አበላት፣ የኢትዮ-ቴሌኮም የስራ ሃላፊዎች፣ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ተገኝተዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቀላጠፈ አገልገሎት እንድናገኝ አስችሏል
Jul 24, 2026 118
ቦንጋ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያልተገባ ወጪንና እንግልትን በማስቀረት የተቀላጠፈ አገልገሎት እንድናገኝ እያስቻለ ነው ሲሉ በቦንጋ ከተማ የማዕከሉ ተገልጋዮች ተናገሩ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ማህበረሰቡ በአቅራቢያው ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተጠቁሟል። በክልሉ ከሚገኙ ስድስት መሶብ የአንድ ማዕከላት መካከል አንዱ በሆነው የቦንጋ ማዕከል ሲገለገሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ዜጎች ከእንግልት የፀዳ ቀልጣፋና ግልፅ አገልግሎት እያገኙ መሆኙን ተናግረዋል።   አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ነስረዲን ኑሩ እና ወጣት ሀይማኖት ታምሩ፤ በማዕከሉ አዲስ ንግድ ፈቃድን በአጭር ደቂቃና ፍጥነት ያለምንም እንግልት ማውጣታቸውን ነው የገለጹት። ይህም ከዚህ ቀደም የነበረውን የተንዛዛ አሰራር በማስቀረት ጊዜያቸውን በአግባቡ መጠቀም እንዳስቻላቸው ጠቁመው፣ በቀጣይ ወደ ማዕከሉ ያልገቡ ተቋማትን በማካተት አገልግሎቱን ማስፋት እንደሚገባም ነው የተናገሩት።   ከዚህ ቀደም የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኝት ብዙ ምልልሶችና እንግልት እንደሚገጥመው ያነሳው ደግሞ ወጣት እምሩ መሸሻ ሲሆን፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማዕከሉ ያለምንም እንግልት አገልግሎት ማግኘቱን ነው የተናግረው። አሰራሩ ከእጅ መንሻ የፀዳ ግልፅና ፈጣን በመሆኑ ከዚህ ቀደም የነበሩ እሮሮዎችን በመፍታት እርካታን የጨመረ በመሆኑ አገልግሎቱን የማስፋት ስራ መጠናከር አለበት ነው ያለው።   የቦንጋ መሶብ የአንድ ማዕከል አልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ አወል አባገሮ ተበታትነው ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ ለህብረተሰቡ ፈጣን፣ ግልፅ እና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ ነው ብለዋል። በማዕከሉ በድምሩ 8 የፌዴራል፣ የከተማ አስተዳደር እና የዞን ተቋማት ተለይተው 44 አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል እየተሰጡ ሲሆን በቀጣይ አገልግሎቱን የማስፋት ስራ ይሰራል ብለዋል። የማዕከሉ ባለሙያዎችም የአገልጋይነት መንፈስ ተላብሰው አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ የተገልጋዮች ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመዋል።   የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና አስተባባሪ አስራት አዳሮ በበኩላቸው፣ በመሶብ የአንድ ማዕከል የሚሰጡ አገልግሎቶች በተለይ ብልሹ አሰራሮችን ማስቀረት የሚያስችሉ ናቸው። በመጀመሪያ ምዕራፍ የተገነባው የክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እስካሁን ከ36 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠቱን ተናግረዋል። ይህን ለማስፋት በተሰጠው ትኩረት አምስት ተጨማሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ተመርቀው ወደ ስራ መግባታቸውን ነው ያነሱት። በአዲሱ በጀት ዓመትም ተጨማሪ 15 መሶብ የአንድ ማዕከላትን የመገንባት ስራ መጀመሩን ጠቁመው፣ ይህም ህብረተሰቡ ከስራው ሳይነጠል በአቅራቢያው ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በአንድ ቦታ ማግኘት ያስችለዋል ብለዋል።
በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 24, 2026 137
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት በከተማዋ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታን በለሚ ኩራ ከፍለ ከተማ ተገኝተው በይፋ አስጀምረዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፥ የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታው ወጣቶችን በክህሎት በማልማት የሀገርን እድገት ለማፋጠን ያለመ ነው ብለዋል። ባለፉት የለውጥ አመታት በመዲናዋ ወጣቶች የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ላይ ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል።   እነዚህ በክህሎትና በቴክኖሎጂ የበቁ ወጣቶች አሁን ላይ ከራሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው አልፈው በሀገር ሁለንተናዊ እድገት ላይ የበኩላቸውን አሻራ እያሳረፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል። አሁን ላይ ወጣቶችን ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ልክ የማብቃት ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። አዲሱ ስማርት ፖሊቴክኒክ የጀርመንን የቴክኒክና ሙያ ልምድ መነሻ በማድረግ፣ በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚገነባና ትውልድ ተሻጋሪ እውቀት የሚገበይበት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኮሌጁ ወጣቶች እውቀትን የሚታጠቁበት፣አዕምሮ እና የሚሰሩ እጆች ተጣጥመው ሀሳብ የሚያፈልቁበት መሆኑን ገልጸዋል። ኮሌጁ በአመት በርካታ አዳዲስ ሰልጣኞችን የመቀበል አቅም እንደሚኖረው ጠቁመው፤ በዘመናዊ ማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሙኒኬሽንና በቴክስታይል ቴክኖሎጂ መስኮች ያሰለጥናል ብለዋል።   ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ፣ በጀትና ጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከተማ አስተዳደሩ በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ በበኩላቸው፤ የሚገነባው ኮሌጅ ወጣቶች በስልጠና ወቅት የሚያመጧቸውን የቴክኖሎጂ ሀሳቦችና የምርምር ውጤቶች ወደ ተግባራዊ ቢዝነስ እንዲቀይሩ፣የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ እንዲመሰርቱና ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ አስጀመሩ
Jul 24, 2026 109
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት ከሰዎች ለሰዎች ድርጅት ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ አስጀምረዋል። የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታው ሲጠናቀቅ ወጣቶችን በማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሪክና ኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሙዩኒኬሽንስ፣ በቴክስታይል እና የሲኤንሲ (CNC) ቴክኖሎጂዎች ላይ ተግባር ላይ ያተኮረ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም ሥልጠና እንደሚሰጥ ከንቲባዋ ገልጸዋል። ሀገርን ማልማት እና ከድህነት መላቀቅ በንድፈ ሐሳብ ብቻ በተገደቡ ትምህርቶች ማሳካት ስለማይቻል፣ ሐሳብን የሚያፈልቁ አዕምሮዎችን እና የሚሠሩ እጆችን ያጣመረ ክህሎት መር የሰው ኃይል እጅግ አስፈላጊ መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አመልክተዋል።   ዛሬ ያስጀመርነው ፕሮጀክት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ወጣቶቻችንን ከሥራ ፈላጊነት ወደ ሥራ ፈጣሪነት፣ ከንድፈ ሐሳብ ወደ ተግባር የሚያሸጋግር፣ አዲስ የሥራ እድል የሚፈጥር የክህሎት ድልድይ የሚሆን ነው ብለዋል። የዚህ ኮሌጅ ግንባታ በጥራትና በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በልዩ ትኩረት የምንከታተለው ይሆናልም ነው ያሉት። ፕሮጀክቱን በትብብር የሚገነባው የረጅም ጊዜ የልማት አጋር የሆነው ሰዎች ለሰዎች ድርጅት እና የሚሠራው ለትውልድ የሚሻገር ዐሻራ ነው በማለት መሬታቸውን ለፕሮጀክቱ የለቀቁ አርሶ አደሮችንም አመስግነዋል።
ስፖርት
የዓለም አትሌቲክስ የአትሌት ትዕግስት አሰፋ የሴቶች ብቻ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን አፀደቀ 
Jul 23, 2026 139
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም አትሌቲክስ የኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ የሴቶች ብቻ (women’s only) የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን ዛሬ ማፅደቁን ይፋ አድርጓል። አትሌት ትዕግስት እ.አ.አ አፕሪል 26 / 2026 በለንደን ማራቶን 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ከ41 ሴኮንድ በመግባት እ.አ.አ በ2025 በራሷ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን በዘጠኝ ሴኮንድ በማሻሻል አሸንፋለች። የዓለም አትሌቲክስ የአትሌቷን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረ ወሰን ዛሬ ማፅደቁን አስታውቋል። የሴቶች ብቻ (women’s only) የዓለም ክብረ ወሰን ሴቶች ብቻ በሮጡበት ውድድር ብቻ የተመዘገበ የዓለም ፈጣን ሰዓት ማለት ነው። የዚህ የዓለም ክብረ ወሰን አመዘጋገብ በሴቶች ውድድር ላይ የወንድ አሯሯጮች ወይም ወንዶች ተቀላቅለው ሲሮጡ (አጠቃላይ ሩጫ) ከሚመዘገበው የዓለም ክብረ ወሰን ጋር የሚለያይ ነው። ወንዶች በሴቶች ውድድር ላይ መኖራቸው የውድድሩን አዝማሚያ እና ሴቶች የሚያስመዘግቡት ሰዓት ላይ ተጽእኖ እንደሚያሳድር የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል። ሴት እና ወንድ ተደባልቀው በሚሮጡበት አጠቃላይ የሴቶች ማራቶን ውድድር የዓለም ክብረ ወሰንን (Overall women's world record) የያዘችው ኬንያዊቷ አትሌት ሩት ቼፕጌቲች ናት። ሩት እ.አ.አ በ2024 በቺካጎ ማራቶን 2 ሰዓት ከ9 ደቂቃ ከ56 ሴኮንድ በመግባት ክብረ ወሰኑን ጨብጣለች። የዓለም አትሌቲክስ ከአትሌት ትዕግስት በተጨማሪ ሰባት የዓለም ክብረ ወሰኖችን ማጽደቁን አስታውቋል። እውቅናና ፈቃድ በተሰጣቸው ውድድሮች ላይ ማሸነፍ፣ የውድድር ሜዳዎቹ የሚፈለገውን መስፈርት ያሟሉ መሆንና አትሌቶች በአበረታች ቅመም ምርምራ ውጤት ጤነኛ መሆናቸው መረጋገጥ አትሌቶች የዓለም ክብረ-ወሰን ባለቤት የሚሆኑባቸው ዋነኛ ቅደመ-ሁኔታዎች ናቸው።
ስፔን አርጀንቲናን በመርታት የዓለም ዋንጫን አነሳች
Jul 20, 2026 406
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ግብ ሳይቆጠርበት በአቻ ውጤት ተጠናቋል። የአርጀንቲና የአማካይ ተጫዋች ኤንዞ ፈርናንዴዝ በ93ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። በ90 ደቂቃ አሸናፊ ባለመገኘቱ ቡድኖቹ ወደ ጭማሪ ሰዓት አምርቷል። ተቀይሮ የገባው ፌራን ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በጨዋታው ስፔን ፍጹም የበላይነት ወስዳለች። የአርጀንቲናው ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ በርካታ ያለቀላቸው ኳሶችን አድኗል። ተጋጣሚዋ አርጀንቲና በጨዋታው ደካማ እንቅስቃሴ አድርጋለች። ቡድኑ የግብ እድል መፍጠር ተስኖታል። ውጤቱን ተከትሎ ስፔን ለሁለተኛው የዓለም ዋንጫን አንስታለች። አውሮፓዊቷ ሀገር እ.አ.አ በ2010 ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 19ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ እንደነበረች ይታወሳል። አርጀንቲና የዓለም ዋንጫ ክብሯን ማስጠበቅ አልቻለችም። ለአራተኛ ጊዜ ዋንጫ የማንሳት ህልሟ አልተሳካም።
አካባቢ ጥበቃ
አረንጓዴ ዐሻራ የሥነ-ምኅዳር ደህንነትን በማስተካከል ዕድገትን በማፋጠን ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው
Jul 23, 2026 174
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የሥነ-ምኅዳር ደኅንነት በማስተካከል ዕድገትን የሚያፋጥን ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን "ተስፋን እንትከል" መሪ ሃሳብ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ ዳርቻ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። በዚሁ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይም፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልጽግና የሚያረጋግጥ ብሔራዊ የልማት ትልም መሆኑን ገልጸዋል። በዘንድሮው መርሃ ግብር ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ሁሉም የማኅብረሰብ ክፍል በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል። በዚሁ መሠረትም የተለያዩ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ ሠራተኞችና የማኅበረሰብ ክፍሎች በየአካባቢያቸው ችግኝ በመትከል ዐሻራቸውን እያኖሩ ይገኛል።   የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አመራርና ሠራተኞችም በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ጎሮ የወንዝ ዳርቻ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። በዚሁ ወቅት የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የሥነ-ምኅዳር ደኅንነት በማጠናከር ዘላቂ ልማትን የሚያፋጥን ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መርሃ ግብሩ በ2011 ዓ.ም ከተጀመረ ወዲህ ባሉት ሰባት ተከታታይ ዓመታት በርካታ ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰዋል። መርሃ ግብሩ የሥነ-ምኅዳር ሚዛንን ከማስጠበቅ ባለፈ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም ዛፍ መትከል ለሰው ልጆች የአዕምሮ እርካታና የልብ ደስታን በመፍጠር ተስፋን የማለምለም አቅም እንዳለው ጠቁመዋል። በተጨማሪም የተተከሉ ችግኞች ፀድቀው ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ መንከባከብና በቀጣይነት መከታተል የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን አሳስበዋል።   በመርሃ ግብሩ የተሳተፉት የምክር ቤቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ተረፈ በዳዳ በበኩላቸው፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከሰው ልጆች ሕይወት ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው የልማት ተግባር ነው ብለዋል። በዚህ ብሔራዊ ዘመቻ ላይ በመሳተፍ አሻራ ማኖር፣ በሀገር ልማትና በትውልድ ተስፋ ላይ አሻራ የማኖር ዕድል መሆኑንም ገልጸዋል። ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መሳተፋቸውን የገለፁት ደግሞ ሌላኛዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የመንግሥታት ግንኙነት፣ የብዝኅነትና የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዳይሬክቶሬት ተጠባባቂ ዳይሬክተር መንደሪን ማርቆስ ናቸው።   መርሃ ግብሩ ለቀጣዩ ትውልድ ልምላሜን የተላበሰች ኢትዮጵያ ለማስረከብ ያለመ በመሆኑ፣ እስካሁን የተከሏቸውን ችግኞች በመንከባከብ እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ የትራንስፖርት ባለሙያ አቶ ኬኔዲ መላኩ በበኩላቸው፣ ከልጅነት ጀምሮ ችግኝ የመትከል ልምድ እንዳላቸው ገልጸዋል።   ይህም ለተፈጥሮ ጥበቃና ለችግኝ እንክብካቤ ያላቸውን ግንዛቤ የበለጠ እንዲጎለብት አስችሎኛል ብለዋል።
የፅዱ ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቭ ከተሞችን ውብ፣ ፅዱ፣ ለኑሮ እና ለቱሪዝም ፍሰት የተመቹ እንዲሆኑ አድርጓል
Jul 23, 2026 205
ባህር ዳር ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡-የፅዱ ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቭ ከተሞችን ውብ፣ ፅዱ ፣ ለኑሮ እና ለቱሪዝም ፍሰት የተመቹ በማድረግ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ማድረጉን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ገለፀ። ''ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ'' በሚል መሪ ሀሳብ የሦስተኛ ዙር ክልል አቀፍ የአካባቢ ብክለት መከላከል ዘመቻ የንቅናቄ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በባህር ዳር ከተማ ተካሂዷል።   የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፍሬነሽ መኩሪያ በመድረኩ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚያስችሉ ስራዎች በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ ይገኛል። በተለይ ከለውጡ ዓመታት ወዲህ የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የሚያስችሉ ወሳኝ ፖሊሲዎችን፣ አዋጆችን፣ መመሪያዎችንና ደንቦችን አውጥቶ በመተግበር ውጤታማ ስራ ማከናወን መቻሉን ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅትም በከተሞች በስፋት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት፣የአረንጓዴ አሻራና መሰል የልማት ስራዎች ለፅዱ ኢትዮጵያ መጠናከር ሰፊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በሃይቆች፣ ወንዞችና ሌሎች የውሃ አካላት ብሎም በመኖሪያ አካባቢዎች ለማሕበረሰቡ ጤና አደገኛ የሆኑ የፕላስቲክ ውጤቶችን በማስወገድ በኩል ምሳሌ የሚሆን ስራ መሰራቱን አረጋግጠዋል። መንግስት የአካባቢ ጥበቃን ለዘላቂ ልማትና መጭውን ትውልድ ታሳቢ በማድረግ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለበለጠ ውጤታማነት በተሻለ ትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ''ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ'' ሦስተኛው ዙር ንቅናቄ የፕላስቲክ ውጤቶችን በማስወገድ፣ የድምፅ ብክለትን በመከላከል እና የብዝሃ ህይወት መመናመን እና የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል በሚያስችሉ ተግባራት ላይ ህብረተሰቡን እያሳተፈ ይገኛል። የአማራ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ኃላፊ አቶ በልስቲ ፈጠነ በበኩላቸው፤ በፅዱ ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቨ በርካታ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን ተችሏል። በተለይም ጣና ሀይቅንና ሌሎች የውሃ አካላትን ከፕላስቲክ ቆሻሻና ሌሎች በካይ ነገሮች በማፅዳት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ነው ያሉት። አሁን ላይ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመሰብሰብና መልሶ መጠቀም የሀብት መፍጠሪያ መሆኑን አመልክተው ፤የአካባቢ ብክለትን በዘላቂነት በመከላከል ምቹ የኑሮ አካባቢ በመፋጠር የተጀመሩ ስራዎች ተጠናከረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። መንግስት በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ከሀገር አልፎ ለአህጉርና ዓለም አቀፋ መድረክ ምሳሌ የሚሆን ስራ እየሰራ ነው ያሉት ደግሞ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ አቶ ይትባረክ አወቀ ናቸው። በፅዱ ኢትዮጵያ ከተሞችን በመግለጥና ለቱሪዝም ዘርፉ ማደግ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅስው ይህ ንቅናቄም በተገቢው መንገድ እንዲተገበርና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል። በመድረኩ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና ከተማ አስተዳደር አመራሮችና ባለሙያዎች ብሎም ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን በባህር ዳር ከተማ የፅዳት ዘመቻና የፓናል ውይይት ተከናውኗል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ከመትከል ባሻገር ለትውልድ የሚተርፍ አርዓያነት ያለው ተግባር ነው
Jul 23, 2026 159
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ከመትከል ባሻገር ለትውልድ የሚተርፍ አርዓያነት ያለው ተግባር መሆኑን የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀይማኖት ዘለቀ ገለጹ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ የዘንድሮውን የክረምት አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በቤላ 18 ቀበሌ የወንዝ ዳርቻ አካሂዷል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሀይማኖት ዘለቀ፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ከመትከል ባለፈ ለመጪው ትውልድ ታሪክ የምናኖርበት አርአያነት ያለው ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። የችግኝ ተከላው የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥን ከመቋቋም እና የግብርና ምርታማነትን ከማሻሻል አንጻር ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ እንዳለውም ተናግረዋል። በመሆኑም ትኩረታችን ችግኝ መትከል ላይ ብቻ ሳይወሰን፤ የተተከሉትን በማሳደግ፣ በመንከባከብ እና የፅድቀት መጠናቸውን በማረጋገጥ ላይ ሊሆን ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።   መርሃ ግብሩ ለምግብ ዋስትና የሚረዱ የፍራፍሬ እና ለአካባቢ ጥበቃ ጠቀሜታ ያላቸው የዛፍ ዝርያዎችን ያካተተ መሆኑንም ገልጸዋል። መገናኛ ብዙሃን መረጃን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ሀገራዊ የደን ሽፋን ጥረትን ለመደገፍ ያላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ባለሥልጣኑ በ8ኛው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 45 ሺህ 125 ችግኞችን ለመትከል አቅዶ እየሰራ ሲሆን፣ እስካሁን በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች ከ43 ሺህ በላይ ችግኞች መተከላቸው ተገልጿል።
ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የእንጦጦ - ቀበናን የወንዝ እና የወንዝ ዳር ፕሮጀክት ጎበኙ
Jul 23, 2026 240
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦የብልፅግና ፓርቲ ዋናው ማዕከል እና የክልል ቅ/ፅህፈት ቤት በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች በመዲናዋ በመፍጠር እና በመፍጠን የተገነቡ የወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክቶችን ተዟዙረዉ ጎብኝተዋል። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዋናው ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ እና ሌሎችም የፌዴራል፣ የአዲስ አበባ እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በጉብኝቱ ተሳትፈዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የብልፅግና ፓርቲ ምናብ ወደ ውጤት እየተቀየረባት የምትገኘው ውቧ መዲናችን ሁሌም አዲስ እየሆነች ትገኘለች ብለዋል። አዲስ አበባ የብልፅግና አይቀሬነት ማሳያ መሆኗን የገለፁት ከንቲባ አዳነች ተግተን በመሥራት በላቁ አዳዲስ ድሎች እንገናኛለን ብለዋል።   በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ በበኩላቸው፤ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች የከተማዋን ገፅታ ከመገንባታቸው ባሻገር የሕዝቡን የኑሮ ደረጃ ከፍ ማድረጋቸውን አስረድተዋል።   ከፍተኛ አመራሮች 10.5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውን፣ አረንጓዴ ቦታዎች፣ የህፃናት መጫወቻዎች፣ የወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ ሱቆች፣ ካፍቴሪያዎች፣ ቤተ መፅሀፍት ፣ የከተማዋ ነዋሪ አንዱ የመዝናኛ ማዕከል የሆነውን የቀበና ግድብ እና ሌሎችም የህዝብ መገልገያዎች ያሉትን የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ ዳር ፕሮጀክትን ተዟዙረዉ መጎብኘታቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 20325
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 13186
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 11978
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 11880
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የአረንጓዴ ዐሻራ፤ ከሥነ-ምኅዳር ዘብ እስከ ዓለም የልማት ተምሳሌት
Jul 23, 2026 341
በመጽሔት አንለይ በወሳኝ ሀገራዊ የልማት ውይይቶች ላይ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸው፣ በዚህም በርካታ ሚሊየን ሄክታር መሬት መታደሱ እንዲሁም የተመዘገበ የደን ሽፋን በአበይት ጉዳይነት ይነሳሉ። ኢትዮጵያ እየተገበረችው ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የአርሶ አደሩ ምርታማነት ማደግ፣ የወጣቱ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን፣ የእናቶች የኑሮ መሻሻልና የተፈጥሮ ሃብት መጠበቅ መቻሉ እንዲሁም የአየር ንብረት መዛባትን ማስተካከልና የደን ሽፋንን ማሳደጉ ለመርሃ ግብሩ ውጤታማነት በአብነትነት ይጠቀሳሉ። በዚህ አተያይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተራ የችግኝ ተከላ ዘመቻ ባሻገር በአካባቢ ጥበቃ፣ በግብርና፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ልማት ዘርፎች መዋቅራዊ ለውጥ በማምጣት አንጸባራቂ ውጤት እያሰገኘ ነው። የዓለም አየር ንብረት ጉዳይ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ባለበት ወቅት፣ አፍሪካ የችግሩ ተጠቂ ብቻ ሳትሆን ለመፍትሄውም የራሷን ልምድና አቅም ማበርከት እንደምትችል እያሳየች ይገኛል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሀገራዊ ንቅናቄም ለአፍሪካ የአካባቢ ጥበቃ ጥረት አዲስ የተግባር ልምድ እየሆነ መጥቷል። የአረንጓዴ ዐሻራው ልዩነት በተተከሉ ችግኞች ቁጥር ብቻ አይለካም። በተራቆቱ መሬቶች ላይ የተመለሰው ሕይወት፣ በገጠር የተፈጠሩ የኢኮኖሚ ዕድሎች፣ የተጠበቁ የውሃ ሀብቶችና ለወደፊት ትውልድ የተገነባው የአካባቢ መሠረት ዋናው ውጤቱ ነው። አረንጓዴ ዐሻራ፤ ከርዕይ ወደ ተግባር!! የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በሀገራዊ ለውጥ ማግስት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በሕዝባዊ ተሳትፎ የተጀመረ ሲሆን፤ እስካሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ከዚህ በፊት የነበረው የተፈጥሮ ሃብት መራቆት በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ብቻ ሳይሆን በዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይም ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ ነበር።   የአፈር መሸርሸር፣ የደን መጥፋትና የድርቅ ተጋላጭነቶችም የገጠር ሥነ-ምኅዳራዊ ሕይወትን ሲፈታተኑ ቆይተዋል። ይህን ምላሽ ለመስጠትም የአረንጓዴ ዐሻራ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማልማትና የደን ሽፋንን ከነበረበት 17 ነጥብ 2 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ በማሳደግ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። የአረንጓዴ አሻራ የኢኮኖሚ ዐሻራ፡- የአረንጓዴ ዐሻራ ትርጉም በአካባቢ ጥበቃ ብቻ አይወሰንም። በኢኮኖሚውም ውስጥ አዲስ የልማት መንገድ እየፈጠረ ይገኛል። በጥምር ግብርና (Agroforestry) አማካኝነት ቡና፣ ፍራፍሬና ሌሎች የኢኮኖሚ ዋጋ ያላቸው ምርቶች ከደን ልማት ጋር እንዲሰናሰሉ አድርጓል። ይህም የገቢ ምንጭን ከማስፋት ባሻገር የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ አስተዋፅዖ አድርጓል። በተለይ የቡና ዘርፍ ከሚሊዮን ወደ ቢሊዮን ዶላር ደረጃ መሻገሩ የዚህ ጥምረት ውጤት አንዱ ማሳያ ነው። የአቮካዶ ምርት ለወጪ ንግድ የፈጠረው ዕድልም አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ ውጤታማነት አብነት ሆኗል። በሌሎች የፍራፍሬ ምርቶች ላይ የመጣው ዕድገት ኢትዮጵያን በዓለም ገበያ የተሻለ ተወዳዳሪ የምትሆንበትን ዕድል ፈጥሯል። ከአፈር ጥበቃ እስከ ምግብ ዋስትና፡- የአረንጓዴ ዐሻራ በአፈር ጤናማነት ላይ ያመጣው ለውጥ የግብርና ምርታማነትን ከፍ አድርጓል። የአፈር ኦርጋኒክ ካርቦን መጨመር፣ የውሃ ማቆየት አቅም መሻሻልና የተፋሰስ ልማት በኢትዮጵያ የመስኖ ልማትና የምግብ ምርት ዕድገት መሠረት ጥለዋል። የስንዴ ምርታማነት ዕድገት እና የቤተሰብ ብልፅግናን የሚያረጋግጥ ስኬታማ ጉዞም የአረንጓዴ ዐሻራ ተጠቃሽ ውጤቶች ናቸው። የተፈጥሮ ጋሻነት፡- ኢትዮጵያ ለድርቅ፣ ለጎርፍና ለመሬት መንሸራተት ተጋላጭ ከሆኑ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ናት። ዛፎችና ስሮቻቸው አፈርን በመያዝ መሸርሸርን ይቀንሳሉ፤ የውሃ ሃብቶችን ጠብቆ በማቆየትና በማሻሻል የድርቅ ተጋላጭነትን የመቋቋም አቅም እየገነባ ነው። በተለይም በርካታ የኃይል ማመንጫ ግድቦችንና የውሃ ሃብቶችን ከደለል አደጋ ለመጠበቅ የደን ልማት ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ እሙን ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም የተፈጥሮ አደጋዎችን በመቀልበስ የተፈጥሮ ጋሻነቱን እያረጋገጠ ይገኛል። የትውልድ ሐውልትና የልማት ውርስ የሆነው አረንጓዴ ዐሻራ!! የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የመንግሥትና የሕዝብ የጋራ ተሳትፎ ውጤት መሆኑን የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ በአንድ ወቅት ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻም፣ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው ዘመቻ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ተሳትፈውበታል። ይህም ኢትዮጵያዊያን የጋራ ታሪክ በመፃፍ በልማት መስክ አስደናቂ የትብብር መንፈስ እንዲገነቡ አስችሏል። የመርሃ ግብሩ ብሔራዊ የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አረንጓዴ ዐሻራ የደን ውድመትን በመከላከል የተፈጥሮ ሃብትን ለመጠበቅ፣ የድርቅና የበረሃማነት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እያስገኘ ነው። የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ተፅዕኖ መቋቋም አዲስ የዲፕሎማሲ ሚና!! በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረክ የአፍሪካ ዋና ጥያቄ የአየር ንብረት ፍትሐዊነት ነው። አህጉሪቱ በአነስተኛ የካርቦን ልቀት ላይ ብትገኝም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ከባድ ጫናን እየተጋፈጠች ይገኛል። በዚህ አውድ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራን እንደ ሀገራዊ ፕሮጀክት በመውሰድ ለአፍሪካ ሀገራት ጭምር የሚጋራ ተሞክሮ ፈጥራለች። የአፍሪካ አህጉራዊ የአየር ንብረት ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄዱም ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ ያላትን ተሳትፎና አመራር ያሳየ ክስተት ነው። ይህ ጉባኤ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የአየር ንብረት ውይይት ማዕከል እንድትሆን ከማገዙም በላይ የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮችን ለማስተናገድ ያላትን አቅም በተግባር አሳይቷል።   ማጠቃለያ፡- የተተከለ ችግኝ፣ የተገነባ ተስፋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ ዳርቻ ''ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት፤ በዚህ ዓመት ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተቀምቷል። በዚሁ ወቅትም ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን ወደ 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በፅናት እየገሰገስን እንገኛለን ብለዋል፡፡ ዘንድሮም የተያዘውን የስምንት ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ስራ ላይ በሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ መትከል ብቻ አይደለም። የኢትዮጵያ የወደፊት የዕድገትና ብልፅግና ማሳኪያ የልማት ትልም እንጂ። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም ከአንድ ችግኝ ጀምሮ እስከ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረክ የደረሰ የሀገር ተሞክሮ ነው። የተተከሉት ችግኞች ዛሬ የአካባቢ ጥበቃ ዘብ ሲሆኑ፣ ነገ ደግሞ የኢኮኖሚ ዕድል፣ የምግብ ዋስትና፣ የኃይል ዘላቂነትና የትውልድ ተስፋ ይሆናሉ። የተተከለው ችግኝ ነገ የሚሆነው ዛፍ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬ፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ጋሻና ለመጪው ትውልድ የሚተላለፍ ሕያው ቅርስ ነው። አረንጓዴ ዐሻራ ዛሬ የሚተከል ተስፋ፣ ነገ የሚሰበሰብ ብልፅግና ነው፤ ተስፋን እንትከል!!!
የሌማት ትሩፋት፡ የኢትዮጵያ ግብርና በአዲስ ምዕራፍ
Jul 22, 2026 313
በሳባ ስለሺ መግቢያ ኢትዮጵያ ለዘመናት የነበራትን የግብርና እምቅ ሀብት ወደ ተጨባጭ የምግብ ዋስትና ለመቀየር ተግዳሮት ሆኖባት የቆየ ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግስት በተጀመረው ዘርፈ-ብዙ የሪፎርም ጉዞ የዘርፉ ታሪክ በተጨባጭ እየተቀየረ ነው። የዚህ ለውጥ አብይ ማሳያ የሆነውና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ ይፋ የሆነው "የሌማት ትሩፋት" መርሃ ግብር አንዱ ነው። ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ የሀገሪቱን የግብርና እና የእንስሳት ሀብት ልማት ጉዞ በአዲስ ምዕራፍ የቃኘ ነው። የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ሲሆን፣ በዋናነት በእንስሳት ሀብት እና ተያያዥ ዘርፎች ላይ ያተኩራል።በእንስሳት ሀብት ልማት ረገድ የወተት ላሞችን፣ የዶሮ (ሥጋ እና እንቁላል)፣ የንብ ማነብ (ማር) እና የዓሣ እርባታን በስፋት የሚያካትት ነው።የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ ኢትዮጵያን ከምግብ ሸማችነት ወደ አምራችነት በማሸጋገር የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ነው። በተለይም በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ፣ የኑሮ ውድነትን በማቃለል፣ የአርሶና አርብቶ አደሩን ገቢ በማሳደግ እንዲሁም ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት የምግብ ሉዓላዊነትን እውን ለማድረግ ያለመ ነው። የሌማት ትሩፋት ለምን አስፈለገ? ፡- የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር፣ ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የተፈጥሮ ሀብትና የሰው ኃይል በመጠቀም፣ ለዘመናት የዘለቀውን የምግብና ሥነ-ምግብ ዋስትና ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተነደፈ ነው። መንግስት ለዚህ መርሃ ግብር ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት የሚገኘውም፣ ሀገሪቱ ያላትን ከፍተኛ የእንስሳት ሀብት በቴክኖሎጂ በመደገፍ ወደ ተጨባጭ እሴትና የሀገር ውስጥ ተጠቃሚነት ለመቀየር እንዲሁም የዘርፉን ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ነው። ባለፉት አራት ዓመታት ምን ተከናወነ?፡- ባለፉት አራት ዓመታት በተተገበረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የወተት፣ የእንቁላል፣ የሥጋ፣ የዓሣ እና የማር ምርቶችን ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ ተከናውኗል። ለዚህ ስኬት በቂና ጥራት ያለው የእንስሳት ተዋጽኦ ለማቅረብ የሚያስችሉ ሰፊ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻልና የማዳቀል ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን፤ የአዳቃይ ቴክኒሻኖችን አቅም መገንባት፣ የፈሳሽ ናይትሮጂን አቅርቦትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለዘርፉ ተዋናዮች ማስተላለፍ ተችሏል። እንዲሁም የእንስሳት መኖ አቅርቦትንና ተደራሽነትን በማስፋፋት፣ የእንስሳት እርባታ ደህንነታቸውን በጠበቀ መልኩ እንዲከናወን በማድረግ እና አስፈላጊውን መሰረተ ልማት በማሟላት ረገድ ላለፉት አራት ዓመታት ቅድሚያ ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል። በመስኩ ምን ተጨባጭ ውጤት ተገኘ ?፡- የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የሀገሪቱን የምግብና ስነ-ምግብ ደህንነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በዜጎች ዘንድ የቆየውን አመለካከት በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ለውጥ አስመዝግቧል። በተለይም በገጠሪቱ የሀገሪቱ ክፍል ብቻ ተወስኖ የነበረውን የግብርና እንቅስቃሴ ወደ ከተሞች በማስፋት፣ ህጻናት፣ እናቶች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ከእንስሳት ተዋጽኦ ማግኘት የሚገባቸውን አስፈላጊ ንጥረ ነገሮች እንዲያገኙ አስችሏል። ይህ ተነሳሽነት የከተማ ግብርናን በማስተዋወቅ ዜጎች በቤታቸው እንስሳትን በማርባት ከራስ ፍጆታ ባለፈ ምርቶቻቸውን ለገበያ በማቅረብ የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል። በመሆኑም፣ ባለፉት ዓመታት በመስኩ የተመዘገቡት ስኬቶች እንደሚያሳዩት፣ መርሃ ግብሩ ዜጎች በተቋማት ተቀጥረው ከመስራት ይልቅ በዘርፉ ተሰማርተው የራሳቸው ስራ ኖሯቸው ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ አድርጓል። ይህ የመንግስት ያላሰለሰ ጥረት፣ የዜጎችን የስነ-ምግብ ፍላጎት ከማሟላት አልፎ፣ ጤናማ እና ሁለንተናዊ ብቃት ያለው ትውልድ በመገንባት ሂደት ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በአሀዛዊ መረጃ የተደገፉ የዘርፉ ስኬቶች ፡- የግብርና ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው አኃዛዊ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በተጀመረ በአራት ዓመታት (2014 ዓ.ም -2018 ዓ.ም) ውስጥ በእንስሳት ምርታማነት አስደናቂ ለውጥ ተመዝግቧል። በወተት ምርት፦ መርሃ ግብሩ ሲጀመር የነበረው 7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ሊትር የማምረት አቅም፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 15 ነጥብ 7 ቢሊዮን ሊትር አድጓል። በእንቁላል ምርት፦ ከነበረበት 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን በከፍተኛ ሁኔታ በማደግ፣ ወደ 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን ከፍ ብሏል። በዶሮ ሥጋ ምርት፦ በ2014 ዓ.ም 90 ሺህ ቶን የነበረው የማምረት አቅም፣ በ2018 ዓ.ም ወደ 253 ሺህ ቶን ከፍ ብሏል። በማር ምርት፦ በ2014 ዓ.ም 146 ነጥብ 7 ሺህ ቶን የነበረው የማምረት አቅም፣ በ2018 ዓ.ም ወደ 428 ሺህ ቶን ከፍ ብሏል። በአሳ ምርት፦ የውሃ አካላትንና ሰው ሰራሽ ኩሬዎችን በአግባቡ በመጠቀም የተከናወነው የአሳ ጫጩት ስርጭት፣ ከ300 ሺህ ወደ 16 ነጥብ 5 ሚሊዮን አድጓል። ይህ ውጤት ሀገሪቱ በእንስሳት ተዋጽኦ ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም በጥቂት ዓመታት ውስጥ እንዴት ማጎልበት እንደተቻለ በግልጽ ያሳያል። ዘርፉ ለውጭ ምንዛሪ ግኝት ምን አበረከተ?፡- የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የሀገር ውስጥ የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢትዮጵያ ከእንስሳት ተዋፅኦ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ አስቻይ ሁኔታዎችን ፈጥሯል። በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ብቻ 24 ነጥብ 2 ሺህ ቶን የተቀነባበረ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን ለዓለም አቀፍ ገበያ በማቅረብ 128 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል። ማጠቃለያ፦ በዘርፉ የተመዘገበውን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ አርብቶ አደር እና አርሶ አደሩ ከተለመደው ባህላዊ የእንስሳት አረባብ ዘዴ ለማላቀቅ የተጀመሩ ስራዎችን ማስቀጠል፣ የእንስሳት መኖ አቅርቦትንና ጤና አገልግሎትን የማዘመን፣ እንዲሁም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅና የማምረት አቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው። በተጨማሪም የመንግስት፣ የግሉ ዘርፍ እና የማህበረሰቡን ቅንጅት ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አሰራር መዘርጋት፣ የቴክኖሎጂ ድጋፍ ያለው የገበያ ትስስር መፍጠርና የደላሎችን ጣልቃ ገብነት ማስወገድ እንዲሁም አምራቹና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ለተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ጠንካራ መሰረት ማኖር ይቻላል። በአጠቃላይ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የግብርና እምቅ ሀብት ወደ ተጨባጭ ሀገራዊ ብልፅግና ለመቀየር የተጀመረ ውጤታማ መንገድ መሆኑን ባለፉት አራት ዓመታት አሳይቷል። ይህ ከተጠናከረ ሀገሪቱ የምግብ ሉአላዊነቷን ለማረጋገጥ ያለመችውን ትልም ከማሳካት የሚያስቆማት ነገር እንደማይኖር አመላካች ነው።    
ሀገራዊ ምክክር፡ለተሻለች ኢትዮጵያ የተከፈተ በር
Jul 22, 2026 202
በኢትዮጵያ ለዓመታት የቆዩ አለመግባባቶችና ችግሮች ብዙ ናቸው።እነዚህ አለመግባባቶች የሀገር ሰላም፤አንድነት፤ልማት እድገትና የዜጎችን የወደፊት ተስፋ የሚፈታተኑ ሆነው ቆይተዋል። አለመግባባቶችን በኃይል ለመፍታት የተደረጉ ሙከራዎች ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጡ አልቻሉም። ስለዚህ የጥላቻን፣የበቀልንና የመከፋፈልን ዑደት ለማቆም የሚያስችል ትክክለኛ መንገድ ውይይት፣መደማመጥና መግባባት መሆኑ በስፋት እየታመነ መጥቷል። በዚህ መነሻ፣ኢትዮጵያ በታሪኳ ታላቅ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እያካሄደች ትገኛለች።ይህ ምክክር ዜጎች ሀሳባቸውን በነፃነት የሚገልጹበትና የጋራ መፍትሄ የሚፈልጉበት መድረክ ሆኗል። የሀገራዊ ምክክሩ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር ሳይሆን፣ የሁሉንም ወገን ድምጽ በማዳመጥ የጋራ መግባባት መፍጠር ነው። ይህ ምክክር በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተወከሉ ዜጎች ድምጽ የሚሰማበት፣አመለካከቶች የሚተነተኑበትና የጋራ መፍትሄዎች የሚፈለጉበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሆኗል። ሀገራዊ ምክክሩ የተለያዩ ወገኖችን በአንድነት በማሰባሰብ፣የከረሙ ችግሮችን በተቀናጀ መንገድ በመፍታት፣ የፖለቲካዊ፣የኢኮኖሚያዊና የማህበራዊ ለውጦችን ለማምጣት ይረዳል። እንዲሁም ኢትዮጵያን ወደ አንድነት፣ሰላምና ብልጽግና ለማሸጋገር የሚያገለግል ታላቅ መድረክ ነው። ሀገራዊ ምክክር ማድረግ ብቸኛው መንገድ ነው ብለው ያመኑ ኢትዮጵያዊያንም ከሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫ እና ከውጭ ጭምር በመምጣት በአዲስ አበባ ተገናኝተው ስለሀገራቸው እየመከሩ ይገኛል። በሁሉም ክልሎች፣በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮችና በውጭ ከሚኖሩ ዜጎች ሕዝብ የወከላቸው ተመካካሪዎችም በንዑስ ቡድኖች በመከፋፈል በተመደቡበት አጀንዳ ላይ መመካከር መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል። በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ሂደት ጠንካራ መግባባትን የሚፈጥር ግልፅና ተስፋ ሰጪ ምክክር እያደረግን ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች በበኩላቸው ገልጸዋል። የሀገራዊ ምክክሩ ስኬት የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን ከመላው ኢትዮጵያዊያን ተሳትፎ ጋር የሚያያዝ ነው። ዛሬ በምክክር የምንገነባው መግባባት፣ነገ ለመጪው ትውልድ የተረጋጋች፣የተባበረች፣ሰላማዊና የበለፀገች ኢትዮጵያን የሚያስረክብ መሠረት ይሆናል። ይህ ሀገራዊ ምክክር የጋራ መግባባት ባህልን ለማጠናከር፤ለፀናችና ለተሻለች ኢትዮጵያ የተከፈተ ትልቅ በር ነው።
የኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነት፤ ራስን ለመቻል የተደረገ ሽግግር
Jul 21, 2026 489
በ አሸናፊ በድዬ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት፣ የብዙኃኑ ዜጋ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆነ የሥራ ዕድል መፍጠሪያ፣ እንዲሁም ለአጠቃላይ ሀገራዊ ዕድገት (ጂዲፒ) ከ33 በመቶ በላይ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሠረታዊ ዘርፍ ነው። ይሁን እንጂ ላለፉት አሥርት ዓመታት የሀገሪቱ ግብርና በዝናብ ጥገኝነት፣ በባህላዊና ኋላ ቀር የሞፈርና ቀንበር የአመራረት ዘይቤ፣ በአፈር መሸርሸር እንዲሁም በዝቅተኛ ምርታማነት ምክንያት የወቅቱን የሕዝብ ቁጥር ዕድገት መመጠንና የዜጎችን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ተስኗት ቆይቷል። ሀገሪቱ በየዓመቱ ለረድኤት እና ለውጭ እርዳታ እጇን እንድትዘረጋ፣ እንዲሁም ለዕለት ጉርስ የሚሆን እህል ከውጭ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንድታስገባ ተገዳ ነበር። ይሁን እንጂ፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት የተጀመሩ ፕሮጀክቶች፣ በእርሳቸው የቅርብ አመራር ሰጪነት የተጀመሩት አዳዲስ ፖሊሲዎችና መዋቅራዊ ማሻሻያዎች ዘርፉን ሙሉ በሙሉ እየቀየሩት ይገኛሉ። ይህ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ የሀገሪቱን ግብርና ከባህላዊና ለዕለት ፍጆታ ብቻ ከሚመረተው የህልውና ግብርና ወደ ዘመናዊ፣ በቴክኖሎጂ ወደታገዘና ከፍተኛ ትርፍ ወደ የሚያስገኝ የንግድ ግብርና እያሸጋገረው ይገኛል። በኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የተመዘገቡ ታሪካዊ ስኬቶችን፣ የምግብ ዋስትናን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት የተወሰዱ ቁልፍ እርምጃዎችን እና የዘርፉን የወደፊት ብሩህ ተስፋዎች እንመልከት፦ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ስኬት ኢትዮጵያ ከሀገራዊ ለውጡ በፊት በየዓመቱ ለስንዴ ፍጆታ ማሟያ የሚሆን እስከ አንድ ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የውጭ ምንዛሬ ታወጣ ነበር። ይህን ከፍተኛ ወጪ ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት እና የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የቆረጠችበት ትልቁና ህያው ማሳያ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ፕሮጀክት ነው። ይህ ተግባር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ልዩ ክትትል፣ የመስክ ምልከታና አነሳሽነት የተጀመረ ሲሆን፣ በአጭር ዓመታት ውስጥ በሀገሪቱ የግብርና ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ተጨባጭ ተአምር ያሳየ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ሆኗል። ሀ. የአመራረት ስር ነቀል ለውጥ ቀደም ሲል ስንዴ በኢትዮጵያ ይመረታል ተብሎ የሚታሰበው በክረምት ዝናብ ብቻ እና በደጋማ አካባቢዎች ነበር። ይህንን የተለመደ አሠራር በመለወጥ፣ በበጋ ወቅት ምንም ዝናብ በሌለበት ያሉትን ወንዞች፣ የውሃ አማራጮችን እና የከርሰ-ምድር ውሃን በመጠቀም በመስኖ የማልማት ሥራ በስፋት ተተገበረ። ይህም አርሶ አደሩ በአንድ መሬት ላይ በዓመት ሁለት እና ሦስት ጊዜ ሰብል እንዲያመርት በማስቻል የምርት ወቅትን በእጥፍ አሳድጎታል። ባህላዊውን ዝናብ ጠባቂነት ወደ ቴክኖሎጂና ውሃ መሪ ግብርና የለወጠ ታሪካዊ ሽግግር ነው። ለ. የመሬት ስፋትና የምርት ዕድገት ፕሮጀክቱ በ2012 ዓ.ም. አካባቢ በጥቂት ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በሙከራ ደረጃ የተጀመረ ቢሆንም፤ በአሁኑ ወቅት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሄክታር መሬቶችን ማሸፈን ችሏል። የመሬት ስፋት አድማስ፦ መጀመሪያ ላይ በደጋማ ቦታዎች ብቻ የነበረው ስንዴ፣ አሁን ላይ ሰፊና ምቹ ሜዳዎች ወደሚገኙባቸው ዝቅተኛና ሞቃታማ የቆላ አካባቢዎች (Lowlands) እንዲስፋፋ ተደርጓል። የምርታማነት መጨመር፦ በኩታ ገጠም (Cluster) እርሻ አሠራር፣ በምርጥ ዘር አቅርቦት እና በሜካናይዜሽን (በትራክተርና ኮምባይነር) አጠቃቀም ምክንያት በሄክታር የሚገኘው የምርት መጠን በአማካይ ከ35 እስከ 45 ኩንታል እና ከዚያ በላይ አድጓል። ይህም በአጠቃላይ ሀገራዊ የስንዴ ምርትን በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኩንታሎች እንዲጨምር አድርጓል። ሐ. ከገቢ ምርት ወደ ውጭ ንግድ፡- ይህ ስልታዊ ስኬት ኢትዮጵያን ለዓመታት ተጭኗት ከነበረው የስንዴ ተረጂነትና ከውጭ የማስገባት ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በኩራት ያላቀቃት ታላቅ ድል ነው። ራስን መቻል፦ ሀገሪቱ በውስጥ ምርቷ ፍላጎቷን ማሟላት መቻሏ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈጠሩ የጂኦፖለቲካ ቀውሶች (ለምሳሌ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ያስከተለው የስንዴ እጥረት) በኢትዮጵያ ላይ የከፋ የምግብ እጥረት እንዳያመጡ ትልቅ ጋሻ ሆኗል። ወደ ውጭ መላክ፦ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ የተረፈውን ምርት ለጎረቤት ምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት እንዲሁም ለዓለም አቀፍ ገበያ በይፋ መላክ የተጀመረበት ታሪካዊ ምዕራፍ ተመዝግቧል። ይህ ስኬት ሀገሪቱ የምግብ ዋስትናዋን በራሷ አቅም ከመገንባቷም በላይ፣ ግብርናን አዲስ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ የኢኮኖሚ ምንጭ እንዲሆን አድርጎታል። የሌማት ትሩፋት" ንቅናቄና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ማለት የዜጎችን ሆድ በካሎሪ (በእህል ምርት) መሙላት ብቻ ሳይሆን፣ የአዕምሮና የአካል እድገትን የሚወስነውን የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ ማለት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በይፋ ያስጀመሩት የሌማት ትሩፋት ሀገራዊ ንቅናቄ ዋና ስትራቴጂካዊ ግብም ይሄው ነው፦ በሀገሪቱ የተመጣጠነ ምግብ በየቤተሰቡ ደረጃ ማሳደግ የታለመለት ግብ ነው።ይህ ንቅናቄ በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ ተገንብቶ ከፍተኛ ስኬት አስመዝግቧል። የእንስሳት ሀብትና የወተት ልማት፦ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀዳሚውን የእንስሳት ሀብት የያዘች ቢሆንም፣ ቀደም ሲል የሚገኘው የወተት ምርት እጅግ ዝቅተኛ ነበር። አራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን የወተት ላሞችን ለማዳቀል የተያዘው እቅድ እየተሳካ ይገኛል። በንቅናቄው ከፍተኛ የወተት ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ በማቅረብ፣ ዘመናዊ የእንስሳት መኖ አጠቃቀምን በማስፋፋት እና በኩታ ገጠም አሠራር የወተት ማቀነባበሪያዎችን በመገንባት የወተት ምርት በዓመት ከሰባት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ወደ 16 ቢሊዮን ሊትር ማሳደግ አስችሏል።   የዶሮና የእንቁላል ምርት ማዕበል፦ በዝቅተኛ ቦታና ወጪ ፈጣን የፕሮቲን ምንጭ ለማግኘት የዶሮ እርባታን ማዘመን ቁልፍ እርምጃ ነበር። በሚሊዮን የሚቆጠሩ የ45 ቀናት የውጭ ድቅል ጫጩቶች ለገጠርና ለከተማ ነዋሪዎች ተሰራጭተዋል። ይህ አሠራር ቀደም ሲል በዓመት ጥቂት እንቁላል ብቻ ከምትጥለው የሀገር ውስጥ ዶሮ ተሻሽሎ፣ በቀጣይነት ለገበያና ለቤት ውስጥ ፍጆታ የሚውል የእንቁላልና የሥጋ ምርትን አሳድጓል። ባለፉት ዓመታት 160 ሚሊዮን ጫጩቶችን ለማሰራጨትና 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን እንቁላል ለማምረት የተያዘው ግብም በውጤታማነት እየተጓዘ ይገኛል።   የንብ ማነብ (የማር ልማት)፦ ኢትዮጵያ ያላትን የበለጸገ የተፈጥሮ ዕፅዋት እምቅ አቅም በመጠቀም ባህላዊ ቀፎዎችን በዘመናዊ ቀፎዎች የመተካት ሥራ በስፋት ተከናውኗል። ይህም በአንድ ቀፎ የሚገኘውን የማር ምርት ከ7 ኪሎ ግራም ወደ 20-30 ኪሎ ግራም በማሳደግ አርሶ አደሩን ተጨማሪ የገቢ ባለቤት አድርጎታል። ለዚህም የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ጉልህ ሚና በማበርከት ላይ ይገኛል።   የአሳ ሀብት ልማት፦ በተፈጥሮ ሐይቆች ላይ ብቻ የነበረውን ጥገኝነት በመስበር፣ በየገጠሩ ሰው ሠራሽ የውሃ ማቆሪያዎችና ኩሬዎችን በመጠቀም የዓሣ እርባታ ተጀምሯል። ይህ ሥራ በተለይ የወንዝ ተፋሰስ ባላቸው አካባቢዎች ማኅበረሰቡ የዓሣ ምርትን በምግብ ሰንሰለቱ ውስጥ እንዲያካትት አግዟል። የብዙኃኑ ተስፋዎች በኢትዮጵያ ግብርና ላይ የመጣው ለውጥ ወቅታዊ ስኬት ብቻ ሳይሆን የወደፊቷን ጠንካራ ሀገር የመገንባት መዋቅራዊ መሠረት ነው። ሀገሪቱ ለዘመናት ከነበረችበት የድርቅና የእርዳታ እህል ጠባቂነት ታሪክ ወጥታ፣ ስንዴን ወደ ውጭ የምትልክ፣ በሌማት ትሩፋት የተመጣጠነ ምግብን የምታረጋግጥ እና አረንጓዴ ዐሻራን በመጠቀም የአየር ንብረቷን የምትጠብቅ ታላቅ ሀገር መሆን እንደምትችል በተግባር አሳይታለች። እነዚህ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሲቀጥሉ፣ የኢትዮጵያ ግብርና የሀገር ውስጥ ፍላጎትን በራስ አቅም ከማሟላት አልፎ የምሥራቅ አፍሪካና የመላው አህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ማዕከል (Breadbasket of Africa) የመሆን ዕቅዷን ሙሉ በሙሉ እውን እንደሚያደርገው ምንም ጥርጥር የለውም።
ትንታኔዎች
የኢትዮጵያዊያን ምክክር፤ የጋራ ነገን የሚያሻግር የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ድልድይ
Jul 22, 2026 308
በሚኪያስ ጎቡ መግቢያ፡- ሀገራት ከጦርነት በላይ የሚፈትናቸው ጠላት አለ፤ እርሱም በአንድ ሀገር ልጆች መካከል የሚፈጠረው የመተማመን መሰናክል ነው። መሣሪያ የፈጠረውን ጉዳት እንደገና መገንባት ይቻላል። የተሰበረ ልብና የጠፋ መተማመን ግን በጉልበት አይመለስም። ለዚህም ነው ብዙ ሀገራት ከግጭት በኋላ ወደ ምክክር የሚመለሱት። ብሔራዊ ምክክር የአንድ መንግሥት ፕሮጀክት ወይም የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአንድ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፈው የሰላም ውርስ ነው። የሚጋጩ ሃሳቦች በጠመንጃ ሳይሆን በቃል ሲገናኙ፣ የተለያዩ ትርክቶች በመደማመጥ ሲቀራረቡ፣ ልዩነቶችም የጥላቻ ምንጭ ሳይሆኑ የመግባባት መነሻ ሲሆኑ ነው እውነተኛ ሀገራዊ ምክክር የሚፈጸመው። የዓለም ተሞክሮ እንደሚያሳየው ብሔራዊ ምክክር አንድ ዓይነት ቀመር የለውም። እያንዳንዱ ሀገር በታሪኩ፣ በባህሉ፣ በፖለቲካዊ እውነታውና በማኅበራዊ መዋቅሩ መሰረት የራሱን መንገድ ይመርጣል። ነገር ግን የሁሉም ግብ አንድ ነው፤ ግጭትን በመግባባት፣ ጥላቻን በመተማመን፣ ፍርሃትን በተስፋ መተካት። በአውሮፓ ከኮሙኒዝም ውድቀት በኋላ፣ በአፍሪካ ከአምባገነናዊ አስተዳደሮች ሽግግር ወቅት፣ በደቡብ አሜሪካ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሂደቶችና በዓረቡ ዓለም ከፖለቲካ አብዮቶች በኋላ የተካሄዱ ምክክሮች አንድ ትልቅ ትምህርት ይሰጣሉ። ምክክር ሲታመን ሀገር ያድናል፤ ለፖለቲካ ጥቅም ሲውል ግን ቀውስን ያባብሳል። ይህ የኢትዮጵያም ትልቁ ፈተና ነው። ሀገራዊ ምክክር የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ወገን ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነት ነው። የምንናገረው ቃል፣ የምንጽፈው ሐሳብ፣ የምናዳምጠው አቋምና የምንቀበለው ልዩነት የነገዋን ኢትዮጵያ ይቀርጻሉ። ምክክር የሚጀምረው በአዳራሽ ሳይሆን በሰዎች ልብ ውስጥ ነው፤ የሚሳካውም ከመናገር በላይ በመደማመጥ ሲቻል ነው። ስለዚህ የዛሬው ጥያቄ "ምክክር ይካሄድ ወይ?" የሚል አይደለም። "ምክክሩን ለሀገር የሚበጅ፣ ለትውልድ የሚተርፍ፣ ለታሪክ የሚያስከብር እንዴት እናድርገው?" የሚለው ነው። መልሱም በአካታችነት፣ በእውነት፣ በመከባበርና በሀገርን ከግል ጥቅም በላይ በማስቀደም ውስጥ ይገኛል። ምክክር፤ የሀገር መድኃኒት ወይስ የትውልድ ፈተና? ምክክር ለምን ያስፈልጋል?፡- ማንኛውም ሀገር የሚያድገው በሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ግንባታ ብቻ አይደለም። በሕዝቦቿ መካከል በሚኖረው መተማመን ጭምር እንጂ። መንገድ፣ ድልድይና ፋብሪካ መገንባት ይቻላል፤ ነገር ግን የተሰበረ ማኅበራዊ ትስስር ካልተጠገነ የልማቱ መሠረት ይናወጣል። ስለዚህ ብሔራዊ ምክክር የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን የሀገር የወደፊት ዕጣ ፋንታ የሚወሰንበት የጋራ አስተሳሰብ ሂደት ነው። የምክክሩ ዋና ዓላማ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር አይደለም። ይልቁንም ሁሉም ወገኖች የራሳቸውን እውነት እየገለጹ፣ የሌላውንም እውነት በማዳመጥ የጋራ መግባባት የሚፈጥሩበት ሂደት ነው። እውነተኛ የምክክር ድል የሚለካውም የማን ሃሳብ አሸነፈ ሳይሆን ለሀገር ምን ያህል ሰላምና መተማመን ፈጠረ በሚለው ነው። የዓለም ተሞክሮ የሚያስተምረን፡- የታሪክ ገጾች እንደሚያሳዩት ሀገራት የብሔራዊ ምክክርን መንገድ የመረጡት ሌሎች አማራጮች ሲያቅቷቸው ነው። አንዳንዶቹ የረዥም ጊዜ የፖለቲካ ቀውስ ነበራቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ በዘር፣ በሃይማኖት ወይም በሥልጣን ሽኩቻ ተከፋፍለው ሲራኮቶ የሰነባበቱ ናቸው። ነገር ግን የተሳካላቸው ሀገራት አንድ የጋራ መርህ ነበራቸው፤ የሀገርን ጥቅም ከፓርቲ፣ ከቡድንና ከግል ጥቅም በላይ አስቀድመዋል። ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ ወደ ዴሞክራሲ የተሸጋገረችው በበቀል ሳይሆን በሰለጠነ ምክክር ነው። ፖላንድና ሀንጋሪ የፖለቲካ ሽግግራቸውን በየጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር አሳልፈዋል። ላይቤሪያና ሊባኖስ የጦርነት ቁስላቸውን ለማዳን የመደማመጥን መንገድ መርጠዋል። በተቃራኒው ግን ምክክርን ለፖለቲካ ሕጋዊነት ማግኛ፣ ለሥልጣን ማራዘሚያ ወይም ለውጭ ጫና ማስታገሻ ብቻ ያደረጉ ሀገራት የበለጠ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። ይህም አንድ ግልጽ ትምህርት ይሰጠናል፤ የምክክር ስኬት የሚወሰነው በመድረኩ ሳይሆን በተመካካሪዎች ቅንነት መሆኑን ያስረዳናል። ምክክር የሚጠይቀው ከባድ ኃላፊነት፡- ሀገራዊ ምክክር የኮሚሽን ወይም የመንግሥት ሥራ ብቻ አይደለም። የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነትን የሚጠይቅ የጋራ ነገ አሻጋሪ ድልድይና የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ነው። ፖለቲከኛው የሀገርን ጥቅም ማስቀደም፣ የሚዲያው እውነትን በሚዛናዊነት ማቅረብ፣ የሲቪክ ማኅበራት የተገለሉ ድምፆችን ማሰማት፣ የኃይማኖት ተቋማት ይቅርታና መቻቻልን ማስፋፋት፣ ወጣቱ ከጥላቻ ይልቅ ውይይትን መምረጥና ምሁራን በማስረጃ የተደገፈ ሃሳብ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ማንም ወገን የራሱን አቋም ብቻ ለማስገደድ ከሞከረ፣ ምክክሩ ወደ ክርክር ይቀየራል። ሁሉም ለመረዳት እንጂ ለማሸነፍ ካልመጡ ደግሞ የምክክሩ መንፈስ ይጠፋል። የሀገራዊ ምክክር ትልቁ ድል የሌላውን አቋም መለወጥ ሳይሆን፣ የሌላውን ህመም መረዳት ነው። ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር፤ ልዩነታቸው ምንድን ነው?፡- ብዙ ጊዜ ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር የሚሉት ቃላት በአንድ ትርጉም ይጠቀሳሉ። ነገር ግን በፖለቲካዊና በማኅበራዊ ሂደቶች እያንዳንዳቸው የተለየ ዓላማና ባህሪ አላቸው። ይህንን ልዩነት አለማወቅ ሀገራዊ ምክክርን ከመጀመሪያው ሊያዛባው ይችላል። ውይይት የሐሳብ ልውውጥ ነው። ሰዎች ስለ አንድ ጉዳይ አመለካከታቸውን ይገልጻሉ፣ ይደማመጣሉ። ሁልጊዜ ውሳኔ ላይ ላይደርስ ይችላል። ክርክር የሚያተኩረው የማን ሃሳብ ትክክል እንደሆነ ላይ ነው። የራስን አቋም በማስረጃ ለማስረዳት ይደረጋል፤ አንድ አሸናፊና አንድ ተሸናፊ ሊኖር ይችላል። ድርድር ደግሞ የጥቅም ግጭትን በመካከለኛ መፍትሔ ለመፍታት የሚደረግ ሂደት ነው። እያንዳንዱ ወገን ከአቋሙ በመቀነስ የጋራ መፍትሔ ለማግኘት ይሞክራል። ሀገራዊ ምክክር ግን ከእነዚህ ሁሉ የላቀ ሂደት ነው። ዓላማው ማንንም ማሸነፍ ወይም ማስሸነፍ ሳይሆን የሀገር የወደፊት አቅጣጫ ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር ነው። በምክክር ውስጥ የሚሸነፍ ሰው የለም፤ የሚያሸንፈው ሀገር ነው። የኢትዮጵያ ልዩ እውነታ፡- ኢትዮጵያ ሦስት ሺህ ዘመናትን የተሻገረ በሕብር ያሸበረቀ ታሪክ፣ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ፣ ቋንቋ፣ ባህልና ኃይማኖት ያላት ሀገር ናት። ይህ በሕብር ያሸበረቀ ልዩነት የኢትዮጵያ ጥንካሬ መሆን ሲገባው በተለያዩ ወቅቶች የፖለቲካ አለመግባባቶችና የታሪክ ትርክቶች የመከፋፈል መሣሪያ ሆነው ቆይተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ ዋና ፈተናም ይህ ነው። ሁሉም የራሳቸውን ታሪክ ይዘው ወደ ጠረጴዛው ይመጣሉ፤ ነገር ግን ከጠረጴዛው የሚወጡት አንድ የጋራ የወደፊት ርዕይ ይዘው መሆን አለባቸው። ይህ ቀላል አይደለም። ስለዚህ ምክክሩ ከቃላት በላይ በተግባር የሚገለጥ ቅንነትን ይፈልጋል። የዋናው ምክክር ጉባኤ የህዝብ ወኪል ተመካካሪዎችም ሀገርን የማስቀደም ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ስኬታማ ምክክር የሚመሰረትባቸው አምስት ምሰሶዎች፡- ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ እንዲሆን ቢያንስ አምስት መሠረታዊ ምሰሶዎች ሊኖሩት ይገባል። እነሱም መተማመን፣ አካታችነት፣ እውነት፣ ፍትሕና የጋራ ርዕይ ናቸው። ከሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበራሰብ የሕዝብ ወኪል 4 ሺ ተመካካሪ ኢትዮጵያዊያንም በሀገር ግንባታ ጉዳይ፣ የመንግስት አደረጃጃትና ስርአት ጉዳይ፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬድዋ ከተሞች ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና የመልካም አስተዳዳር ጉዳዮች፣ የሰላም ግንባታ ጉዳዮች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽ ማዕከል እየመከሩ ይገኛል። ሀገራዊ ምክክር ያለፈውን ለመቁጠር ሳይሆን፣ የወደፊቱን ለመገንባት የሚደረግ የጋራ ጉዞ ነው። የኢትዮጵያ መንገድም የልዩነት ግድግዳን የሚያፈርስ የትውልድ አደራና የብሔራዊ መግባባት ማሰሪያ ጥበብና ትልም ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፤ የተገኙ ዕድሎች፣ ዋና ፈተናዎች እና የወደፊት አቅጣጫ በታሪክ ጉዞዋ ውስጥ ኢትዮጵያ ብዙ የፈተና ዘመናትን አልፋለች። አንዳንዶቹ ፈተናዎች ከውጭ ጥቃት የመጡ ቢሆኑም፣ አብዛኞቹ ግን ከውስጣዊ አለመግባባቶች፣ ከተለያዩ የታሪክ ትርክቶች፣ ከፖለቲካ ፉክክርና ከመተማመን እጥረት የተፈጠሩ ናቸው። ስለዚህ የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደት የዛሬን ችግር ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፣ የትውልድ ዕዳን ለማቃለል የተጀመረ ታሪካዊ ሂደት ነው። ይህ ሂደት ቀላል አይደለም። በርካታ ዓመታት የተከማቹ ቅሬታዎች፣ የተለያዩ እውነታዎች፣ የተቃራኒ ትርክቶችና የተለያዩ የፖለቲካ ፍላጎቶች በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መገናኘታቸው በራሱ ትልቅ ፈተና ነው። ነገር ግን ከዚህ በላይ ትልቁ ፈተና ልዩነትን ወደ መግባባት መቀየር ነው። ዕድሎች፤ ሊጠቀሙባቸው የሚገቡ ወሳኝ መስኮቶች፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት ኢትዮጵያ ለብዙ ዓመታት ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ የምታነሳበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። የታሪክ አተረጓጎም፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የሥልጣን ክፍፍል፣ የሀብት አጠቃቀም፣ የፍትሕ ጉዳዮችና የአብሮነት ዕሴቶች በጦርነት ሳይሆን በሐሳብ የሚፈቱበት ዕድል ይፈጥራል። ከዚህም በላይ ምክክሩ የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር የሚያስችል ዕድል ነው። ለብዙ ዓመታት "አሸናፊና ተሸናፊ" በሚለው አስተሳሰብ የተመራውን ፖለቲካ ወደ "አብሮ ማሸነፍ" የሚሸጋግር ከሆነ እውነትም የኢትጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ ጠንካራ መሠረት ያገኛል። በሂደቱ ፊት የሚቆሙ ፈተናዎች፡- ማንኛውም ሀገራዊ ምክክር ከፍተኛ ተስፋ እንደሚፈጥር ሁሉ ከባድ ፈተናዎችንም ይዞ ይመጣል። የመጀመሪያው ፈተና የመተማመን እጥረት ነው። ለብዙ ዓመታት የተገነባ ጥርጣሬ በጥቂት ወራት አይጠፋም። ስለዚህ የምክክሩ ተዓማኒነት በእያንዳንዱ እርምጃ ሊገነባ ይገባል። ሁለተኛው ፈተና የተለያዩ የታሪክ ትርክቶች ናቸው። አንድ ክስተት በአንዱ ወገን የድል ታሪክ ሲሆን፣ በሌላው ወገን የመከራ ታሪክ ሊሆን ይችላል። ይህን ልዩነት በክብር መቀበል እንጂ መግፋት አይቻልም። በሌላ መልኩም የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ ስርጭት ነው። በዲጂታል ዘመን አንድ ያልተረጋገጠ መረጃ በጥቂት ደቂቃዎች ሺዎችን ሊደርስ ይችላል። ስለዚህ የሚዲያ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሚወስዱት ኃላፊነት ከመቼውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። የምሁራንና የመገናኛ ብዙኅን ሚና፡- በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ምሁራን ስሜትን ሳይሆን ማስረጃን ማቅረብ አለባቸው። የማኅበረሰብ ችግሮችን በሳይንሳዊ ጥናት መተንተን፣ ከሌሎች ሀገራት ልምድ መማርና አማራጭ መፍትሔዎችን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። መገናኛ ብዙኅንም በዚህ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና አላቸው። መገናኛ ብዙኅን ወሬን ከማባዛት ይልቅ እውነትን ማጣራት፣ ልዩነትን ከማባባስ ይልቅ መግባባትን ማጎልበት፣ ስሜትን ከማቀጣጠል ይልቅ እውነታን ማቅረብ አለበት። ምክክሩን የሚያጠናክር የመገናኛ አውታር ታሪክ ይሠራል፤ የሚያደናቅፍ ደግሞ በታሪክ ይጠየቃል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ቀን የሚጠናቀቅ ክስተት አይደለም። ምክክር በትውልድ የሚገነባ የፖለቲካ ባህል ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራውን ሊጨርስ ይችላል፤ ነገር ግን የመደማመጥ ባህል በሕዝብ ውስጥ ካልሰረጸ የምክክሩ እውነተኛ ዓላማ አይሳካም። የዛሬ ውሳኔ፤ የነገ ኢትዮጵያ፡- አንዳንድ የታሪክ ወቅቶች በየቀኑ አይመጡም። አንዳንድ ውሳኔዎችም የአንድ መንግሥት ዘመንን ብቻ ሳይሆን የትውልዶችን ዕጣ ፈንታ ይወስናሉ። ሀገራዊ ምክክር የእነዚህ ታሪካዊ ውሳኔዎች አንዱ ነው። ዛሬ በምንመርጠው የምክክር ባህል፣ በምንገነባው መተማመንና በምናሳየው የፖለቲካ ብስለት ላይ የነገዋን የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ተምሳሌት ኢትዮጵያ ያንፃል። ምክክር ሁሉንም ችግር በአንድ ጊዜ የሚፈታ አስማታዊ መፍትሔ አይደለም። ነገር ግን ጦርነትን ከውይይት፣ ጥላቻን ከመቻቻል፣ መከፋፈልን ከመተባበር የሚተካ ብልህ መንገድ ነው። የሚያደርገውም ልዩነቶችን ማጥፋት ሳይሆን ልዩነቶችን በአንድ ሀገር ጣሪያ ስር እንዴት እንደሚኖሩ የጋራ ሕግና ሥርዓት መፍጠር ነው። በእርግጥ ኢትዮጵያ ከባድ ፈተናዎችን አሳልፋለች። የፖለቲካ አለመተማመን፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የፀጥታ ችግሮች፣ የኢኮኖሚ ጫናዎችና የማኅበራዊ ስብራቶች በቀላሉ የሚያልፉ አይደሉም። ይሁን እንጂ እነዚህን ችግሮች በጥይት ከመፍታት ይልቅ በምክክር ለመፍታት መሞከር በራሱ የታሪክ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ ግን የአንድ ተቋም ብቻ አይደለም። የመንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኅን ተቋማት፣ የምሁራን፣ የወጣቶች፣ የሴቶችና የእያንዳንዱ ዜጋ የጋራ ኃላፊነት ነው። የሀገር ዕጣ ፋንታ ለአንድ ቡድን ብቻ የሚተው አይደለም፤ በጋራ የሚገነባ እንጂ። ከምክክር ወደ ባህል፡- ምክክሩ ተጠናቀቀ ማለት የሀገሪቱ ችግሮች ተፈቱ ማለት አይደለም። እውነተኛው ስኬት የሚለካው የመደማመጥ ባህል በማኅበረሰቡ ውስጥ ሲሰርጽ ነው። በትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በመገናኛ ብዙኅን፣ በፖለቲካ ተቋማትና በየቤቱ የመነጋገር ባህል ካልጠነከረ፣ ምክክሩ የሰነድ ውጤት ብቻ ሆኖ ይቀራል። የእውነተኛ ዴሞክራሲ መሠረት ተመሳሳይ አስተሳሰብ መኖር አይደለም፤ የተለያዩ አስተሳሰቦችን በሰላም የመቀበል ባህል መኖር ነው። ልዩነት የችግር ምንጭ ሳይሆን የጥንካሬ ምንጭ ሲሆን ነው አንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም የምታገኘው። የማጠቃለያ፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት የሚያስፈልገው ብልህ አመራር ብቻ አይደለም፤ ታጋሽ ዜጎችንም ይፈልጋል። ሀገር የምትገነባው በግንብ ሳይሆን በመተማመን ነው። ሰላም የሚጸናውም በፍርሃት ሳይሆን በፍትሕ ነው። ዛሬ የምንመርጠው የምክክር መንገድ ነገ ለልጆቻችን የምንተወው ታሪክ ይሆናል። ስለዚህ በኢትዮጵያን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተደራጅተው የሚመከርባቸው ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የዛሬ አጀንዳ ብቻ አይደሉም፤ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚቀርጽ የትውልድ አደራ እንጂ። የዋናው ምክክር ጉባኤ ተመካካሪ የሕዝብ ወኪሎችም ከግልና ቡድን ፍላጎት ይልቅ የቀጣዩን ትውልድና ሀገርን ማስቀደም ይጠበቅባቸውል። ምክክር የቃላት ልውውጥ ብቻ አይደለም፤ የተሰበረ መተማመንን የሚጠግን፣ የተከፋፈለ ማኅበረሰብን የሚያቀራርብ፣ የትውልድ ታሪክን በአዲስ ተስፋ የሚጽፍ ሀገራዊ ጥበብ ነው። የምንወስነው ዛሬ የምንወርሰውን ነገ ይበይናል። ምክክር የሀገር መድኅን ነው፤ ኢትዮጵያም እየመከረች ነው።      
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 503
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 4493
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!  
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 3618
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 10672
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 20869
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 13901
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 19654
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 102165
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 77279
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 56338
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 53893
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 38788
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 38448
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 37932
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 36799
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 102165
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 77279
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 56338
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 53893
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 6990
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 4807
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም