ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች ነው
Oct 13, 2025 61
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ገለጹ፡፡ በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስተባባሪነት በአረንጓዴ ትራንስፖርትና በታዳሽ ኃይል ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች የአዳማ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተጎብኝቷል፡፡ በጉብኝቱ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን፣ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰንን ጨምሮ ከኢትዮጵያ እና ኬንያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ ኩባንያዎች ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴዔታ በርኦ ሀሰን በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የትራንስፖርት ዘርፉን ጨምሮ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ ባከናወነቻቸው ተግባራት በርካታ ለውጦችን አስመዝግባለች ብለዋል፡፡ ለዚህም በሕዳሴ ግድብ፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብርና በንፋስ ኃይል ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች ትልቅ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዘርፉን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅና ከአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የጸዳ እንዲሆን ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል፡፡ መንግሥት ታዳሽ ኃይል የሚጠቀም የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍን እውን ለማድረግ ጠንካራ የፖሊሲ ድጋፍ ስለማድረጉ አንስተዋል። በዚህም በርካታ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በማንሳት፥ ባለሀብቶችም በዘርፉ ኢንቨስት እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና መንግስት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓት የተሰማሩ ተቋማትን እንደሚያበረታታ አረጋግጠዋል፡፡   በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለዓለም ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ናቸው ብለዋል፡፡ በተለይ ደግሞ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ የወሰደው እርምጃ ይበል የሚባል ነው ብለዋል፡፡ ሀገራቸው ይህንን ተግባር እንደምትደግፍም አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ሳምንት ከነገ ጥቅምት 4 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 6 ቀን 2018 በአዲስ አበባ ይካሔዳል፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ የብዙሃን ትራንፖርት፣ ባቡር፣ ኮሪደር ልማት፣ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች እንዲሁም በፖሊሲ ረገድ እያከናወነች ያለችውን ተጨባጭ ሥራ እንደምታቀርብም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ጉዞ ዓለም በሚያየውና በሚመሰክረው ሀገራዊ ስኬት የተደገፈ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Oct 13, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየው፣ በሚዳስሰውና በሚመሰክርላቸው ስኬቶች የተደገፈ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ። 18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ’’ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነትና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል።   በዚሁ ወቅት ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፤ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ፍቅር፣ ክብርና ቃል ኪዳን በልባቸው የሚያድሱበት የጋራ ማንነታቸውን የሚያጎለብቱበትና የነገ ተስፋን የሚያጸኑበት ነው ብለዋል። ክብረ በዓሉ ያለፈውን የጀግንነት ገድል፣ የዛሬውን የልማት ጥረት፣ የነገውን የዕድገትና ብልጽግና ትልም በማጣመር ፈጣን ዕድገት ለምታስመዘግበው ኢትዮጵያ ድል አብሳሪና የጉዞ ህያው ምስክር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን የህልውና ፈተናዎች በህዝቦቿ የአንድነት ብርቱ ክንድ በጽናት ተሻግራ የራሷን ዕድል የመወሰን ብቃት እያስመሰከረች መሆኗንም አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየውና በሚዳስሰው ብሎም በሚመሰክርላቸው ሀገራዊ ስኬቶች የተደገፈ ነው ብለዋል።   የዚህ ብስራት መቅረዝና ከፍታም የዘመናት ህልም የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ የሀገርንና ቀጣናዊ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪ የደም ስር ለመሆን መብቃቱን ገልጸዋል። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ከብርሃን ምንጭነት ባሻገር ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሲቆሙ ታላላቅ ሀገራዊ የልማት ገድሎችን ማስመዝገብ እንደሚቻል በተግባር የተረጋገጠበት የሉዓላዊነት ማህተም መሆኑን ተናግረዋል። በአረንጓዴ ዐሻራም በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች መትከሏን አስታውሰው፤ ይህም የኢትዮጵያን ገጽታ በመቀየርና ለዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ በማበርከት ዓለም አቀፍ ከበሬታና ሞገስ ያስገኘላት የልማት ገድል ነው ብለዋል።   የዕድገት ጉዟችን ቀጣይ ምዕራፍ የኢኮኖሚ ብርታትን ማረጋገጥ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታውም በግብርና ምርታማነት የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከውጭ ከሚገባ የማዳበሪ ጥገኝነት በማላቀቅ ሀገራዊ ኢኮኖሚን የሚያጠናክር ታላቅ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ጋዝ ሃብትን በመጠቀም ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለኃይል ምንጭነት እንዲውል የማድረግ ውጥንም በአዲስ የኃይል ምንጭ የኢኮኖሚ ዕድገትና ብልጽግና ጉዞን እንደሚያፋጥን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ለወጣቶች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩና የሀገርን የከፍታ ዘመን በማይናወጥ መሠረት ለማስቀመጥ እንደሚረዱ ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ውጤታማነት ለማስቀጠልም በልዩነት ውስጥ ያለን ወርቃማ ውበት በማክበር የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ዘላቂ ሰላም መሠረት እየጣለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የሚከበረው በጠንካራ አንድነትና በበለጸገ ኢኮኖሚ ላይ ማቆም ሲቻል እንደሆነም አስገንዝበዋል። ለዚህም ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ትብብር ላይ የተመሰረተ ፍትሐዊ የባሕር በር የማግኘትና የመጠቀም መብታችን በሰላማዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና በሰጥቶ መቀበል መርህ ማስከበራችን ይቀጥላል ብለዋል። ኢትዮጵያውያንም በአዕምሯቸው ሰላምን በማጽናት በልባቸው የተስፋ ወጋገን አጥብቆ በመያዝ በክንዳቸው ብርታትም ሠንደቅ ዓላማና ሀገራቸውን መጠበቅ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ ኢኖቬተሮች እና ስራ ፈጣሪዎች እየተሳተፉበት የሚገኘው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ሁነት በዱባይ እየተካሄደ ነው
Oct 13, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- 45ኛው የገልፍ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) ዛሬ በዱባይ ዓለም አቀፍ የንግድ ማዕከል ተጀምሯል። “የዳታ ማዕከላት በነገ ዲጂታል መሰረተ ልማቶች ግንባታ ውስጥ ያላቸው ቁልፍ ሚና” የአውደ ርዕዩ መሪ ሀሳብ ነው። በዓለም ላይ ግዙፍ ከሚባሉት የቴክኖሎጂ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ጀማሪ ስራ ፈጠራ ትዕይንቶች አንዱ በሆነው ጂአይቴክስ ከ180 ሀገራት የተወጣጡ ከ6 ሺህ 500 በላይ አቅራቢዎች፣ 1 ሺህ 800 ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች እና 1 ሺህ 200 ባለሀብቶች ተሳታፊ ሆነዋል። ጂአይቴክስ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች፣ የመንግስት ተቋማት፣ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ኢኖቬተሮች እና ተመራማሪዎችን በአንድ መድረክ ያገናኘ ነው።   ዓለም አቀፍ አውደ ርዕዩ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት፣ የጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ኢኖቬሽን፣ የጤና እና ባዮ ቴክኖሎጂዎች፣ ኮሙኒኬሽን፣ ሮቦቲክስ፣ የቀጣዩ ትውልድ ቴክኖሎጂዎች፣ የኮምፒዩተር ስርዓቶች እና ማሽኖችን ጨምሮ በርካታ ዘርፎችን ይዟል። በጂአይቴክስ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች እና ባለሀብቶች እየተሳተፉ እንደሚገኙ Pulse of Africa ሚዲያ ከስፍራው ዘግቧል። እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው ዓለም አቀፍ ሁነት በዋናነት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ መሰረት ያደረጉ ፈጠራዎች እንደሚቀርቡና በዘርፉ ላይ ትኩረት ያደረጉ ውይይቶች እንደሚካሄዱም ተመላክቷል። እንደ ተባበሩት መንግስታት የንግድ እና ልማት ጉባዔ (አንክታድ) ጥናት ከሆነ እንደ አውሮፓውያኑ የዘመን ቀመር በ2033 የሰው ሰራሽ አስተውሎት ገበያ ወደ 4 ነጥብ 8 ትሪሊዮን የአሜሪካን ዶላር ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል። አሁን ላይ የ757 ነጥብ 58 ቢሊዮን ዶላር የገበያ ድርሻ እንዳለው ይገመታል። አንክታድ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቴክኖሎጂ ገበያው ያለው ድርሻ ወደ 29 በመቶ ማደጉን ጠቅሶ፤ ይህም ኤአይ በዘርፉ እያደገ የመጣውን ከፍተኛ አቅም የሚያመላክት ነው። ይህ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቀጣይ ጊዜያት በዓለም ላይ የሚኖረውን ተፅእኖ ያሳያል። የገልፍ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) እ.አ.አ 1981 አንስቶ እየተካሄደ የሚገኝ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ሁነት ነው።
በአማራ ክልል ግልጽና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ችሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተጀመረው ተግባር ይጠናከራል-የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት
Oct 13, 2025 56
ባህር ዳር፤ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)-በአማራ ክልል ግልጽና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ችሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተጀመረው ተግባር ተጠናከሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ። በክልሉ በክረምት የዳኞች የእረፍት ጊዜ ምክንያት ዝግ ሁኖ የቆየው የችሎት አገልግሎት ዛሬ ተጀምሯል። በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ አደራ በችሎት አገልግሎት ማስጀመሪያ ሥነ ስርአት ላይ እንደገለጹት፣ ከክልል እስከ ወረዳ ባሉ ፍርድ ቤቶች መደበኛ የችሎት አገልግልት ዛሬ መሰጠት ተጀምሯል።   በፍርድ ቤቶች የሚሰጠው መደበኛ የችሎት ተግባር ቀልጣፋ እንዲሆን ባለፈው ዓመት በዲጂታል የታገዘ የችሎት ሥራ መጀመሩን ጠቁመው፤ አገልግሎቱም የተገልጋዩን ገንዘብ፣ ወጪና እንግልት ይቀንሳል ብለዋል። በዲጂታል የታገዘ የችሎት ሥራን በማስፋፋት የተገልጋይን ጊዜ፣ ወጪና ገንዘብ ለመቀነስ የተጀመረው ተግባር በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክረምት ወቅት በተካሄደ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ የዲጂታል ችሎትን በተሟላ መልኩ ለማስኬድ የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውንም አውስተዋል። ባለፈው በጀት ዓመት የእድሳት ሥራ የተከናወነለት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሕንጻ የዳኝነት ስርዓቱን ቀልጣፋና ጊዜውን የሚመጥን ለማድረግ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አቶ ሀብታሙ አስገንዝበዋል። ዲጂታል አሰራሩ ባለጉዳዮች ዞን በሚገኙ ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ሆነው ወደክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሳይመጡ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት የሚያገኙበት ስርአት ለመዘርጋት መቻሉንም ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪ ህብረተሰቡ ነጻ፣ግልጽና ተአማኒነት ያለው ፍትህ አግኝቶ እርካታን ለመፍጠር እንደሚያስችል አስረድተዋል።      
የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ ይገባል
Oct 13, 2025 61
አርባ ምንጭ፣ዲላ፣ ቦንጋ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ) :- የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንደሚገባ ተመላከተ። 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሐሳብ በቦንጋ፣ ዲላና አርባ ምንጭ ከተሞች በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል። በቦንጋ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ላይ መልእክት ያስተላለፉት የካፋ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ግርማ ደፋር የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ስናከብር በየዘመኑ ለሀገር ነፃነትና ክብር የተከፈለውን ዋጋ በማሰብ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር ሉዓላዊነትና የነፃነት ምልክት መሆኑን ጠቅሰው ክብሩን በሚመጥን የስራ ትጋት በርትቶ በመስራት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገር ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ሰነድ ያቀረቡት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ንጉሴ ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው ለሰንደቅ ዓላማ ከፍታ የተከፈለው ዋጋ የማይረሳና በየዘመኑ እየተዘከረ የሚኖር መሆኑን ገልፀዋል። የቀኑ መከበር ሀገራዊ እሴቶችን አጠናክሮ ለትውልድ በማስተላለፍ አንድነታችንንና ህብረታችንን በማጠናከር ህብረ-ብሔራዊነትን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፣ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ምልክትና የሉዓላዊነት መገለጫ መሆኑን አንስተው ቀኑ ከሌሎች በዓላት በተለየ መልኩ በሰፊው መከበር እንዳለበት አንስተዋል። በአርባ ምንጭ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወላይቴ ቢቶ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር መለያ፣ የሉዓላዊነትና የአንድነታችን መገለጫ ነው ብለዋል፡፡ የሃገሪቱን የማንሠራራት ጉዞ ለማስቀጠልም ሁሉም በተሰማራበት መስክ ሰንደቅ ዓላማን ከፍ የሚያደርግ ተግባር መፈጸም እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ በተመሳሳይም በዲላ ከተማ በዓሉ ሲከበር የጌዴኦ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ምስጋና ዋቃዮ እንዳሉት ቀኑ ህገ መንግስታዊ መሰረት ያለውና ህብረተሰቡን በቅንነት ለማገልገል ዳግም ቃላችንን የምናድስበት ነው። የህብረ ብሔራዊትንና ሉዓላዊነት መገለጫ የሆነውን ሰንደቅ ዓላማ ማክበርና ማጉላት እንደሚገባም አመልክተዋል። ሰንደቅ ዓላማ የሃገራችን ኩራትና ነጻነት በመሆኑ የሚገባውን ክብር ልንሰጠው ይገባል ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጠቅ ዶሪ በተሰማራንበት ዘርፍ ውጤታማ በመሆን የሰንደቅ ዓላማ ክብርን ማጎልበት እንደሚገባም አንስተዋል።  
የሚታይ
የኢትዮጵያ ጉዞ ዓለም በሚያየውና በሚመሰክረው ሀገራዊ ስኬት የተደገፈ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Oct 13, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየው፣ በሚዳስሰውና በሚመሰክርላቸው ስኬቶች የተደገፈ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ። 18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ’’ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነትና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል።   በዚሁ ወቅት ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፤ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ፍቅር፣ ክብርና ቃል ኪዳን በልባቸው የሚያድሱበት የጋራ ማንነታቸውን የሚያጎለብቱበትና የነገ ተስፋን የሚያጸኑበት ነው ብለዋል። ክብረ በዓሉ ያለፈውን የጀግንነት ገድል፣ የዛሬውን የልማት ጥረት፣ የነገውን የዕድገትና ብልጽግና ትልም በማጣመር ፈጣን ዕድገት ለምታስመዘግበው ኢትዮጵያ ድል አብሳሪና የጉዞ ህያው ምስክር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን የህልውና ፈተናዎች በህዝቦቿ የአንድነት ብርቱ ክንድ በጽናት ተሻግራ የራሷን ዕድል የመወሰን ብቃት እያስመሰከረች መሆኗንም አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየውና በሚዳስሰው ብሎም በሚመሰክርላቸው ሀገራዊ ስኬቶች የተደገፈ ነው ብለዋል።   የዚህ ብስራት መቅረዝና ከፍታም የዘመናት ህልም የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ የሀገርንና ቀጣናዊ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪ የደም ስር ለመሆን መብቃቱን ገልጸዋል። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ከብርሃን ምንጭነት ባሻገር ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሲቆሙ ታላላቅ ሀገራዊ የልማት ገድሎችን ማስመዝገብ እንደሚቻል በተግባር የተረጋገጠበት የሉዓላዊነት ማህተም መሆኑን ተናግረዋል። በአረንጓዴ ዐሻራም በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች መትከሏን አስታውሰው፤ ይህም የኢትዮጵያን ገጽታ በመቀየርና ለዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ በማበርከት ዓለም አቀፍ ከበሬታና ሞገስ ያስገኘላት የልማት ገድል ነው ብለዋል።   የዕድገት ጉዟችን ቀጣይ ምዕራፍ የኢኮኖሚ ብርታትን ማረጋገጥ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታውም በግብርና ምርታማነት የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከውጭ ከሚገባ የማዳበሪ ጥገኝነት በማላቀቅ ሀገራዊ ኢኮኖሚን የሚያጠናክር ታላቅ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ጋዝ ሃብትን በመጠቀም ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለኃይል ምንጭነት እንዲውል የማድረግ ውጥንም በአዲስ የኃይል ምንጭ የኢኮኖሚ ዕድገትና ብልጽግና ጉዞን እንደሚያፋጥን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ለወጣቶች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩና የሀገርን የከፍታ ዘመን በማይናወጥ መሠረት ለማስቀመጥ እንደሚረዱ ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ውጤታማነት ለማስቀጠልም በልዩነት ውስጥ ያለን ወርቃማ ውበት በማክበር የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ዘላቂ ሰላም መሠረት እየጣለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የሚከበረው በጠንካራ አንድነትና በበለጸገ ኢኮኖሚ ላይ ማቆም ሲቻል እንደሆነም አስገንዝበዋል። ለዚህም ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ትብብር ላይ የተመሰረተ ፍትሐዊ የባሕር በር የማግኘትና የመጠቀም መብታችን በሰላማዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና በሰጥቶ መቀበል መርህ ማስከበራችን ይቀጥላል ብለዋል። ኢትዮጵያውያንም በአዕምሯቸው ሰላምን በማጽናት በልባቸው የተስፋ ወጋገን አጥብቆ በመያዝ በክንዳቸው ብርታትም ሠንደቅ ዓላማና ሀገራቸውን መጠበቅ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ ኢኖቬተሮች እና ስራ ፈጣሪዎች እየተሳተፉበት የሚገኘው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ሁነት በዱባይ እየተካሄደ ነው
Oct 13, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- 45ኛው የገልፍ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) ዛሬ በዱባይ ዓለም አቀፍ የንግድ ማዕከል ተጀምሯል። “የዳታ ማዕከላት በነገ ዲጂታል መሰረተ ልማቶች ግንባታ ውስጥ ያላቸው ቁልፍ ሚና” የአውደ ርዕዩ መሪ ሀሳብ ነው። በዓለም ላይ ግዙፍ ከሚባሉት የቴክኖሎጂ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ጀማሪ ስራ ፈጠራ ትዕይንቶች አንዱ በሆነው ጂአይቴክስ ከ180 ሀገራት የተወጣጡ ከ6 ሺህ 500 በላይ አቅራቢዎች፣ 1 ሺህ 800 ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች እና 1 ሺህ 200 ባለሀብቶች ተሳታፊ ሆነዋል። ጂአይቴክስ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች፣ የመንግስት ተቋማት፣ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ኢኖቬተሮች እና ተመራማሪዎችን በአንድ መድረክ ያገናኘ ነው።   ዓለም አቀፍ አውደ ርዕዩ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት፣ የጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ኢኖቬሽን፣ የጤና እና ባዮ ቴክኖሎጂዎች፣ ኮሙኒኬሽን፣ ሮቦቲክስ፣ የቀጣዩ ትውልድ ቴክኖሎጂዎች፣ የኮምፒዩተር ስርዓቶች እና ማሽኖችን ጨምሮ በርካታ ዘርፎችን ይዟል። በጂአይቴክስ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች እና ባለሀብቶች እየተሳተፉ እንደሚገኙ Pulse of Africa ሚዲያ ከስፍራው ዘግቧል። እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው ዓለም አቀፍ ሁነት በዋናነት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ መሰረት ያደረጉ ፈጠራዎች እንደሚቀርቡና በዘርፉ ላይ ትኩረት ያደረጉ ውይይቶች እንደሚካሄዱም ተመላክቷል። እንደ ተባበሩት መንግስታት የንግድ እና ልማት ጉባዔ (አንክታድ) ጥናት ከሆነ እንደ አውሮፓውያኑ የዘመን ቀመር በ2033 የሰው ሰራሽ አስተውሎት ገበያ ወደ 4 ነጥብ 8 ትሪሊዮን የአሜሪካን ዶላር ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል። አሁን ላይ የ757 ነጥብ 58 ቢሊዮን ዶላር የገበያ ድርሻ እንዳለው ይገመታል። አንክታድ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቴክኖሎጂ ገበያው ያለው ድርሻ ወደ 29 በመቶ ማደጉን ጠቅሶ፤ ይህም ኤአይ በዘርፉ እያደገ የመጣውን ከፍተኛ አቅም የሚያመላክት ነው። ይህ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቀጣይ ጊዜያት በዓለም ላይ የሚኖረውን ተፅእኖ ያሳያል። የገልፍ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) እ.አ.አ 1981 አንስቶ እየተካሄደ የሚገኝ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ሁነት ነው።
በክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው - አቶ አብርሃም ማርሻሎ
Oct 13, 2025 65
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለፁ። የክልሉ የሥራና ክህሎት ቢሮ ባካሄደው የሴክተር ጉባኤ አቶ አብርሃም እንደገለጹት በክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጎልበት የዜጎች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።   ‎በዚህም በተለይ ወጣቶች ተወዳዳሪ በመሆንና የተሻለ ሀብት በመፍጠር ረገድ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ነው የገለጹት። ‎የአካባቢን የልማት አቅም በመለየትና ወጣቶችን በቂ ክህሎት በማስጨበጥ እሴት በሚጨምሩ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው ተጠቃሚ የሚሆኑበት መደላድል የመፍጠር ሥራው በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በጉባኤው የተገኙት ሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በበኩላቸው እንዳሉት እንደ ሀገር ብቁ የሰው ኃይል በማፍራትና ዘላቂና አስተማማኝ የሥራ ዕድል በመፍጠር ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።   ክህሎት መር በሆነ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ እንዲሁም በተቋም ግንባታ ላይ የሪፎርም አጀንዳዎችን በመቅረጽ የተለያዩ ሥራዎች እተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። በዚህም ላለፉት ተከታታይ አራት ዓመታት በአማካይ በዓመት 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር እንደተቻለ ጠቅሰው፣ በቀጣይም ይህን ለማጠናከር ትኩረት ተደርጓል ብለዋል። በሲዳማ ክልል ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት የሚበረታታ መሆኑን ጠቅሰው የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የሲዳማ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረፅዮን አበበ ከ2015 ዓ.ም በፊት የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው ክህሎትን ዋንኛ ትኩረት ያደረገ ባለመሆኑ በዘርፉ የሚፈለገው ውጤት ሳይመዘገብ ቆይቷል።   ባለፉት ሁለት ዓመታት አንድም ዜጋ ያለ በቂ ክህሎትና ሥልጠና ወደሥራ እንዳይገባ አቅጣጫ ተቀምጦ ሲሰራ መቆየቱንም አመልክተዋል፡፡ ይህም ቀደም ሲል የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ላይ ይስተዋል የነበረው የውጤት ማጣት፣ የመበተን፣ የመሰላቸት እና ሀብት መፍጠር ያለመቻል ችግር ተፈትቶ ውጤት መታየት መጀመሩን ገልጸዋል። እንደ ቢሮ ኃላፊዋ ገለፃ በ2017 በጀት ዓመት በመደበኛ ሥልጠና ከ30 ሺህ በላይ እንዲሁም በአጫጭርና ገበያ ተኮር ሥልጠናዎች ከ61 ሺህ በላይ ዜጎችን ማሰልጠን ተችሏል ፡፡ በሥልጠና ተቋማት፣ በአገልግሎት መስጫ እና በሥራ ማዕከላት ላይ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥርዐትን በመዘርጋትም ዘርፉን የማዘመን ሥራም ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። በመድረኩ በተያዘው ዓመት በዘርፉ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ባለፈው በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና አጋር አካላት የዕውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል፡፡  
የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን ቀድሞ መከላከልና በራስ አቅም ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የተቀናጀ አቅም እየተገነባ ነው
Oct 13, 2025 72
ሰመራ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን ቀድሞ መከላከልና በራስ አቅም ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የተቀናጀ አቅም እየተገነባ መሆኑን የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሸነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) ገለጹ። ዓለም አቀፍ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ቀን "ለአደጋ ስጋት አይበገሬነት ግንባታ ትኩረት እንስጥ" በሚል መሪ ሃሳብ በአፋር ክልል በሰመራ ከተማ ተከብሯል።   በሁነቱ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሸነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር)፤ አደጋዎችን ለመከላከልና በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት በሁሉም ረገድ ዝግጁ መሆን ይገባል ብለዋል። በተለይም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ምጣኔ ሃብት መገንባት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።   በተፈጥሮ የሚመጡ አደጋዎችን ቀድሞ የመከላከልና በራስ አቅም ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የተቀናጀ አቅም መፍጠር እንደሚገባ አንስተው ለዚህም ዘላቂና የተቀናጀ አሰራር መፍጠር ያስፈልጋል ነው ያሉት። በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ፤ በተለይም የግብርና ልማት ስራዎችን በማስፋትና ምርታማነትን በማሳደግ ለአደጋዎች ጥንቃቄና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባት እንደሚገባ ገልጸዋል። የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ሀገራዊ የኢኮኖሚ አቅምን በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ማረጋገጥ የጋራ አጀንዳ ሆኖ በተጠናከረ መልኩ መቀጠል አንዳለበትም አስገንዝበዋል።   በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የአፋር ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኀላፊ አሊ መሐመድ፤ በክልሉ የሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ቀድሞ የመከላከልና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅም ለመፍጠር እየተሰራ ነው ብለዋል። የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ የአደጋ ተጋላጭነትን የመቀነስ ስትራቴጂና ምርታማነትን የማሳደግ ስራም እንዲሁ። በመርሃ ግብሩ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የአደጋ ስጋት አመራሮች ተሳትፈዋል።
ብሔራዊ የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኅብረብሄራዊ አንድነት እንዲጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Oct 13, 2025 66
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ ብሔራዊ የወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኅብረብሄራዊ አንድነት እንዲጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሙና አህመድ ገለጹ። ሚኒስትር ዴኤታዋ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ብሔራዊ በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ መስኮች የኀብረተሰቡን ተጠቃሚነት ከፍ ያደረጉ ውጤቶች እየተገኘበት ነው። በአቅመ ደካሞች ቤት እድሳትና ግንባታ፣ የጤና ምርመራና ህክምና፣ በትራፊክ አገልግሎት፣ በማዕድ ማጋራትና ሌሎች ዘርፎች በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ለውጡን ተከትሎ ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተሰጠው ትኩረት ትልልቅ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን ጠቅሰው በኀብረተሰቡ ዘንድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ባህል እየሆነ መምጣቱንም አንስተዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከኢኮኖሚ ጠቀሜታዎች ባሻገር የእርስ በእርስ ትስስር እንዲጎለብት አወንታዊ ሚና እየተጫወተ ነውም ብለዋል። በተለይም ብሔራዊ የወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኅብረብሄራዊ አንድነት እንዲጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አንዱ የሌላውን እሴት እና ባህል እንዲያውቅ በማድረግ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጠናከር በማድረግ በኩል የላቀ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ዘላቂ ለማድረግ በአሰራር የማስደገፍ ሥራ በትኩረት እየተከናዋነ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ደኤታዋ ብሄራዊ የበጎ ፈቃድ ፖሊሲን ሥራ ላይ ለማዋል እየተሰራ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል። ፖሊሲው አስፈላጊው ግበዓት ከተሟላለት በኋላ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ሥራ ላይ እንደሚውልም አብራርተዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ውጤታማነት ለማሳደግ በቴክኖሎጂ በታገዘ አሠራር የማስደገፍ ጉዳይ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አመልክተዋል። በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጠቀሜታዎች ባለፈ ለጥቅል ሀገራዊ ምርት ያለውን አስተዋጽኦ መለካት የሚያስችል መስፈርት እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልጸዋል። መስፈርቱን ለማዘጋጀት የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮዎች ተቀምሮ በግብዓትነት መወሰዱን ጠቁመው በዘርፉ የተሻለ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ዓይነተኛ ሚና እንዳለውም አስረድተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ጉዞ ዓለም በሚያየውና በሚመሰክረው ሀገራዊ ስኬት የተደገፈ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Oct 13, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየው፣ በሚዳስሰውና በሚመሰክርላቸው ስኬቶች የተደገፈ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ። 18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ’’ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነትና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል።   በዚሁ ወቅት ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፤ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ፍቅር፣ ክብርና ቃል ኪዳን በልባቸው የሚያድሱበት የጋራ ማንነታቸውን የሚያጎለብቱበትና የነገ ተስፋን የሚያጸኑበት ነው ብለዋል። ክብረ በዓሉ ያለፈውን የጀግንነት ገድል፣ የዛሬውን የልማት ጥረት፣ የነገውን የዕድገትና ብልጽግና ትልም በማጣመር ፈጣን ዕድገት ለምታስመዘግበው ኢትዮጵያ ድል አብሳሪና የጉዞ ህያው ምስክር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን የህልውና ፈተናዎች በህዝቦቿ የአንድነት ብርቱ ክንድ በጽናት ተሻግራ የራሷን ዕድል የመወሰን ብቃት እያስመሰከረች መሆኗንም አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየውና በሚዳስሰው ብሎም በሚመሰክርላቸው ሀገራዊ ስኬቶች የተደገፈ ነው ብለዋል።   የዚህ ብስራት መቅረዝና ከፍታም የዘመናት ህልም የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ የሀገርንና ቀጣናዊ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪ የደም ስር ለመሆን መብቃቱን ገልጸዋል። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ከብርሃን ምንጭነት ባሻገር ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሲቆሙ ታላላቅ ሀገራዊ የልማት ገድሎችን ማስመዝገብ እንደሚቻል በተግባር የተረጋገጠበት የሉዓላዊነት ማህተም መሆኑን ተናግረዋል። በአረንጓዴ ዐሻራም በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች መትከሏን አስታውሰው፤ ይህም የኢትዮጵያን ገጽታ በመቀየርና ለዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ በማበርከት ዓለም አቀፍ ከበሬታና ሞገስ ያስገኘላት የልማት ገድል ነው ብለዋል።   የዕድገት ጉዟችን ቀጣይ ምዕራፍ የኢኮኖሚ ብርታትን ማረጋገጥ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታውም በግብርና ምርታማነት የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከውጭ ከሚገባ የማዳበሪ ጥገኝነት በማላቀቅ ሀገራዊ ኢኮኖሚን የሚያጠናክር ታላቅ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ጋዝ ሃብትን በመጠቀም ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለኃይል ምንጭነት እንዲውል የማድረግ ውጥንም በአዲስ የኃይል ምንጭ የኢኮኖሚ ዕድገትና ብልጽግና ጉዞን እንደሚያፋጥን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ለወጣቶች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩና የሀገርን የከፍታ ዘመን በማይናወጥ መሠረት ለማስቀመጥ እንደሚረዱ ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ውጤታማነት ለማስቀጠልም በልዩነት ውስጥ ያለን ወርቃማ ውበት በማክበር የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ዘላቂ ሰላም መሠረት እየጣለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የሚከበረው በጠንካራ አንድነትና በበለጸገ ኢኮኖሚ ላይ ማቆም ሲቻል እንደሆነም አስገንዝበዋል። ለዚህም ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ትብብር ላይ የተመሰረተ ፍትሐዊ የባሕር በር የማግኘትና የመጠቀም መብታችን በሰላማዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና በሰጥቶ መቀበል መርህ ማስከበራችን ይቀጥላል ብለዋል። ኢትዮጵያውያንም በአዕምሯቸው ሰላምን በማጽናት በልባቸው የተስፋ ወጋገን አጥብቆ በመያዝ በክንዳቸው ብርታትም ሠንደቅ ዓላማና ሀገራቸውን መጠበቅ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።
የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ ይገባል
Oct 13, 2025 61
አርባ ምንጭ፣ዲላ፣ ቦንጋ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ) :- የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንደሚገባ ተመላከተ። 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሐሳብ በቦንጋ፣ ዲላና አርባ ምንጭ ከተሞች በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል። በቦንጋ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ላይ መልእክት ያስተላለፉት የካፋ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ግርማ ደፋር የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ስናከብር በየዘመኑ ለሀገር ነፃነትና ክብር የተከፈለውን ዋጋ በማሰብ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር ሉዓላዊነትና የነፃነት ምልክት መሆኑን ጠቅሰው ክብሩን በሚመጥን የስራ ትጋት በርትቶ በመስራት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገር ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ሰነድ ያቀረቡት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ንጉሴ ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው ለሰንደቅ ዓላማ ከፍታ የተከፈለው ዋጋ የማይረሳና በየዘመኑ እየተዘከረ የሚኖር መሆኑን ገልፀዋል። የቀኑ መከበር ሀገራዊ እሴቶችን አጠናክሮ ለትውልድ በማስተላለፍ አንድነታችንንና ህብረታችንን በማጠናከር ህብረ-ብሔራዊነትን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፣ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ምልክትና የሉዓላዊነት መገለጫ መሆኑን አንስተው ቀኑ ከሌሎች በዓላት በተለየ መልኩ በሰፊው መከበር እንዳለበት አንስተዋል። በአርባ ምንጭ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወላይቴ ቢቶ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር መለያ፣ የሉዓላዊነትና የአንድነታችን መገለጫ ነው ብለዋል፡፡ የሃገሪቱን የማንሠራራት ጉዞ ለማስቀጠልም ሁሉም በተሰማራበት መስክ ሰንደቅ ዓላማን ከፍ የሚያደርግ ተግባር መፈጸም እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ በተመሳሳይም በዲላ ከተማ በዓሉ ሲከበር የጌዴኦ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ምስጋና ዋቃዮ እንዳሉት ቀኑ ህገ መንግስታዊ መሰረት ያለውና ህብረተሰቡን በቅንነት ለማገልገል ዳግም ቃላችንን የምናድስበት ነው። የህብረ ብሔራዊትንና ሉዓላዊነት መገለጫ የሆነውን ሰንደቅ ዓላማ ማክበርና ማጉላት እንደሚገባም አመልክተዋል። ሰንደቅ ዓላማ የሃገራችን ኩራትና ነጻነት በመሆኑ የሚገባውን ክብር ልንሰጠው ይገባል ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጠቅ ዶሪ በተሰማራንበት ዘርፍ ውጤታማ በመሆን የሰንደቅ ዓላማ ክብርን ማጎልበት እንደሚገባም አንስተዋል።  
ሠንደቅ ዓላማችንን በክብር ለትውልድ ለማስተላለፍ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት ተግተን መስራት አለብን - ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)
Oct 13, 2025 61
ቦንጋ/ወላይታ ሶዶ/ወልቂጤ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፡- ሠንደቅ ዓላማችንን በክብር ለትውልድ ለማስተላለፍ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት ተግተን መስራት አለብን ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። 18ኛው የሠንደቅ ዓላም ቀን በቦንጋ፣ በወላይታ ሶዶና ወልቂጤ ከተሞች በድምቀት ተከብሯል። በቦንጋ በተከበረው በዓል ላይ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ፤ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረ ሰቦችና ሕዝቦች ህብር መገለጫ የሆነውን ሠንደቅ ዓላማን በክብር መጠበቅ እንደሚገባ ተናግረዋል።   በቀደምት አያቶቻችን አኩሪ ገድል ተጠብቆ የቆየውን ሠንደቅ ዓላማችንን በክብር ለትውልድ ለማስተላለፍ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት ተግተን መሠራት አለብን ብለዋል። የቀኑ መከበር ለሠንደቅ ዓላማ መስዋእትነት የከፈሉ ጀግኖችን ለማሠብና ለትውልዱ ለማስተላለፍ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የገለጹት ደግሞ የካፋ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ግርማ ደፋር ናቸው። ሁሉም ዜጋ በተሠማራበት መስክ ሕዝቡን በታማኝነትና በቅንነት ለማገልገል በየዓመቱ ቃሉን የሚያድስበት መሆኑንም አመልክተዋል። ሠንደቅ ዓላማ ክብርና መለያችን ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ፖሊስ አባል ኮማንደር በድሩ ማሞ ናቸው። ቀደምት አያቶቻችን በክብር ያስረከቡንን ሠንደቅ ዓላማ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ተግተን እንሠራለን ብለዋል። በተመሳሳይ በዓሉ በወላይታ ሶዶ በተከበረበት ወቅት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ፤ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ጀግኖች አያቶች የሀገርን ነፃነት ያስከበሩበት ምልክት መሆኑን ተናግረዋል። የዘንድሮው የሠንደቅ ዓላማ ቀን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተመረቀበት እንዲሁም ሌሎች ታላላቅ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅት መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው አውስተው፤ ይህም የስኬቶቻችን ከፍታ ማሳያ ነው ብለዋል።   በርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተመስገን ጌታቸው፤ ሠንደቅ ዓላማ የኢትዮጵያዊነት መገለጫ ነው ብለዋል። ሁላችንም በየተሠማራንበት ጠንክረን በመስራት የህዳሴ ግድብን እንዳሳካን ሁሉ ሌሎችንም የጋራ ፕሮጀክቶች በመፈፀም ደምቀን ለመታየት ትጋታችንን አጠናከረን መቀጠል አለብን ሲሉ ተናግረዋል። በርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት የስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ዳይሬክተር አሠለፈች መብራቱ ፤ ሠንደቅ ዓላማ ከኢትዮጵያዊያን አልፎ ለሌሎች አፍሪካዊያንም የከፍታ ዘመን ማሳያ ዓርማ ነው ብለዋል። ይህንን ደግሞ ህዝቡን በታማኝነትና በሐቀኝነት በማገልገል እንዲሁም በሁሉም ዘርፎች መልካም አስተዳደርን በማስፈን የሠንደቅ ዓላማን ክብር በተግባር ለመግለጽ እየሠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በዓሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተከበረበት ወቅት የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ መነቴ ሙንዲኖ ፤ ጀግኖች አያቶቻችን የነፃነት ምልክት የሆነውን ሠንደቅ ዓላማ ለአዲሱ ትውልድ ማስረከባቸውን ተናግረዋል። ትውልዱም አብሮነቱንና ሀገራዊ አንድነቱን በማጠናከርና ልማትን በማፋጠን ኢትዮጵያን ከፍ የማድረግ አደራውን ማጠናከር አለበት ብለዋል።
የግብጽ የእኔ ብቻ ልጠቀም ባይነት ዘመን አክትሟል፤ በናይል ወንዝ አጠቃቀም አዲስ የትብብር ምዕራፍ ተከፍቷል
Oct 13, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፡- የግብጽ የእኔ ብቻ ልጠቀም ባይነት ዘመን አብቅቶ በናይል ወንዝ ላይ በጋራ የመልማት አዲስ የትብብር ምዕራፍ ተከፍቷል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ግብጽ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና የአባይ ወንዝ ዙሪያ የምታደርጋቸውን ጠብ አጫሪ ንግግሮች በጽኑ አውግዟል። ግብጽ በቅኝ ግዛት ዘመን ውሎች የብቸኛ ተጠቃሚነት አባዜ መጠመዷን እንደቀጠለችበት አመልክቷል። የግብጽ ከፍተኛ ባለስልጣን ሀገራቸው በናይል ተፋሰስ ሀገራት በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ የውሃ ጉድጓድ መቆፈሪያ እና የዝናብ መሰበብሰቢያ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ አነስተኛ ይዞታ ያላቸውን ፕሮጀክቶችን በመገንባት ከአፍሪካ ጋር አጋርነቷን እያሳየች ነው ማለታቸው እውነተኛ የቀጣናዊ ትብብር ፍላጎት ማሳያ አለመሆኑንም ገልጿል። እውነተኛ የአፍሪካ አጋርነት በውሃ ሀብቶች ፍትሃዊነት እና እኩልነትን በመጠቀም ማመንና የሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት የመልማት መብትን እውቅና መስጠትን የሚጠይቅ መሆኑንም ሚኒስቴሩ በመግለጫው አመላክቷል። ግብጽ በናይል ወንዝ ጊዜው ያለፈበትን የታሪካዊ መብቶች እሳቤ የሙጥኝ ብላ መቀጣሏን ገልጾ፤ ይህም ዓለም አቀፍ ህግን ያላከበረና የተፋሰሱን ሀገራት ህጋዊ መብቶች ከግምት ውስጥ ያላስገባ መሆኑን አብራርቷል። የኢትዮጵያ መንግስት የናይል ወንዝ የመልማት መብቷን በመጠቀም እያደገ የመጣውን የኢነርጂ እና የውሃ ፍላጎቶቿን ለመመለስ እያከናወነች ያለውን ስራ በየትኛውም አይነት ጫና እንደማታቆምና አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታውቋል። ሚኒስቴሩ በመግለጫው ግብጽ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እና የናይል ቤዚን የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ላይ ስታደርጋቸው የነበሩ ድርድሮች ታማኝነት የጎደላቸው እንደነበሩም ገልጿል። የናይል ቤዚን የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት በተፋሰሱ ሀገራት መካከል ብቸኛ የጋራ የውሃ ተጠቃሚነት ማዕቀፍ መሆኑንም አስረድቷል። ኢትዮጵያ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሁሌም ዝግጁ መሆኗንም ገልጿል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የመልማት መብት እና ቀጣናዊ ትብብር መገለጫ መሆኑንም ሚኒስቴሩ በመግለጫው አስታውቋል። ማስፈራሪያዎችንና ከመሰረታዊ የትብብር እሳቤዎች ያፈነገጡ አካሄዶችን በማቆም ከሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት ጋር በጋራ መከባበር እና ፍትሃዊ መርሆዎች አብሮ መስራት እንደሚገባ አመላክቷል። ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ዘላቂ አጠቃቀም ላይ ከተፋሰሱ አገራት ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኗንም ነው ሚኒስቴሩ በመግለጫው ያረጋገጠው።
ሰንደቅ ዓላማ የሀገር አንድነት ማስጠበቂያ ብሔራዊ ዓርማ ነው
Oct 13, 2025 91
አምቦ/ ነቀምቴ ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፡- ሰንደቅ ዓላማ የአገር አንድነት ማስጠበቂያ ብሔራዊ ዓርማና የነጻነታችን ምልክት ነው ሲሉ የሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ የስራ አመራሮች እና ሰራተኞች ተናገሩ። 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የኢንዱስትሪው ሰራተኞችና አመራሮች በተገኙበት ተከብሯል። በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኮሎኔል ስለሺ ነገራ፣ ሰንደቅ ዓላማ የነጻነት ምልክት ነው ብለዋል። የሰንደቅ ዓላማ ቀን ስናከብር ለሀገር አንድነት እና ሉዓላዊነት ዋጋ የከፈሉትን በማሰብ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ነጻነት ምልክት መሆኑን ገልጸዋል። የዛሬው ትውልድም የቀደምት አያቶች ፈለግ ተከትሎ የሀገር ሉዓላዊነት እና አንድነትን ለማስጠበቅ ከፊት መሰለፍ አለበት ሲሉም ተናግረዋል። ከበዓሉ ተሳታፊዎች ሌተናል ኮሎኔል ጌቱ ብርሃኑ በበኩላቸው ሰንደቅ ዓላማ የሀገር አንድነት ማስጠበቂያ ብሔራዊ አርማ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ቀደምት ጀግኖች አባቶች ሀገርን በክብር ያወረሱን ለሰንደቅ ዓላማ ባላቸው ፍቅር መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬው ትውልድም ለዚህ በጎ ዓላማ መቆም አለበት ብለዋል። ሀምሳ አለቃ አዲሱ ጉዲና፣ ለሰንደቅ ዓላማ ክብር እና ለሀገር ሉዓላዊነት የሚጠበቅባቸውን መሰዋእትነት ለመክፈል ምንጊዜም ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ምክትል አስር አለቃ ላቀች ሙሉዓለም ወታደር በጀግንነት ወጥቶ ለሀገሩ ዳር ድንበር መስዋትነት የሚከፍለው ለሰንደቅ ዓላማ በመታመኑ እንደሆነ ጠቅሰው፤ ለስንደቅ ዓላማ ክብር ሁሉም ዘብ መቆም አለበት ነው ያሉት። በተመሳሳይ በነቀምቴ ከተማ የሰንደቅ ዓላማ ቀን አካባበር ላይ የተገኙት የነቀምቴ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መሰረት ታደሰ እንደተናገሩት ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር መገለጫ ነው ብለዋል። የሀገርን ክብር እና ሉዓላዊነት ለማስከበር ቀደምት አባቶች ብዙ ዋጋ ከፍለዋል ያሉት አፈ ጉባኤዋ አሁን ያለው ትውልድም በልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ሀገር ወዳድነቱን ማረጋገጥ አለበት ብለዋል። የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ ተወካይ ረዳት ፕሮፌሰር መላኩ ጌታሁን በበኩላቸው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ስናከብር ሀገራችን የጀመረችውን የልማት ስራዎች በመደገፍ ለውጤታማነቱ በመረባረብ መሆን አለበት ሲሉ ገልጸዋል።  
ሠንደቅ ዓላማ መላው ኢትዮጵያውያንን ለጋራ ዓላማ የሚያሰባስብ ዓርማ ነው
Oct 13, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ሠንደቅ ዓላማችን መላው ኢትዮጵያውያንን ለጋራ ዓላማ የሚያሰባስብ የማንነት መገለጫ ዓርማ ነው ሲሉ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ ገለጹ። አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ 18ኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን "ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ" በሚል መሪ ሐሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል፡፡   በዚሁ ወቅት የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ሀገርን ከወራሪዎች ለመከላከልና ነጻነትን ለማስጠበቅ ሲደረግ የነበረው ተጋድሎ ምልክት መሆኑን አስገንዝበዋል። የመረጃና ደኅንነት ተቋሙ አባላትም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ ሉዓላዊነትና ክብር ለማስጠበቅ በሚያደርጉት ስምሪት የሠንደቅ ዓላማውን ትልቅ አደራ በልባቸው በመያዝ በከፍተኛ የሀገር ፍቅር መንፈስ እስከ መስዋዕትነት ድረስ ዋጋ ይከፍላሉ ብለዋል፡፡   ሠንደቅ ዓላማው መላው ኢትዮጵያውያንን ለጋራ ዓላማ የሚያሰባስብ የማንነት መገለጫ ዓርማ ነው ማለታቸውን አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመላክቷል። ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተወጣጡትና በኅብረ-ብሔራዊ ስብጥር ለአንድ ሀገራዊ ዓላማ የተሰለፉት የተቋሙ አባላትም፤ በሠንደቅ ዓላማው ጥላ ስር ሀገራዊ ደኅንነትን የማረጋገጥ ተልዕኮን በላቀ መንፈስ የሚወጡ መሆኑን አስታውቀዋል። በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በተከበረው 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ተሳትፈዋል።
የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት ሀገር የመገንባት አቅም የሚጎለብትበት የማንሠራራት ጉዞ ዓርማ ነው - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Oct 13, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ፈተናዎችን በጽናት በመሻገር አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት ሀገር የመገንባት አቅም የሚጎለብትበት የማንሰራራት ጉዞ ዓርማ መሆኑን የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን ’’ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነትና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል።   የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በዚሁ ወቅት፤ በሕገ መንግስቱና በሠንደቅ ዓላማ አዋጅ ድንጋጌ መሠረት የሠንደቅ ዓላማ ቀን በጥቅምት ወር መጀመሪያ ሳምንት ሰኞ በየዓመቱ ይከበራል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ የዜጎች የብዝሃነት፣ የእኩልነትና የሕብረብሔራዊ አንድነት መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል። የሠንደቅ ዓላማ ቀንም ለሠንደቅ ዓላማችን ልንሰጠው የሚገባውን ክብር የምናድስበት፣ ቃልኪዳናችንን የምናጸናበትና ብሔራዊ የአርበኝነታችንን የምንቀሰቅስበት ነው ብለዋል።   ለሠንደቅ ዓላማ ቀን የተሰጠው መሪ ሀሳብም የዛሬውን ተግባር፣ የነገውን ምኞትና ትልም በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማም የውስጥና የውጭ ጠላቶች ሊሰብሩት የማይችሉት የሕብረብሔራዊ አንድነትና የሉዓላዊነት ምሽግ መሆኑን አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ፈተናዎችን በጽናት በመሻገር አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት ሀገር የመገንባት አቅም የሚጎለብትበትና ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚታይበት የማንሰራራት ጎዞ ዓርማ መሆኑን አንስተዋል። ሠንደቅ ዓላማችን በታሪክ ውጣ ውረዶች ውስጥ የጽናታችን ምልክት ነው ያሉት አፈጉባኤ ታገሠ፤ ዛሬም በዘላቂ ልማትና ብልጽግና ወደ ብሩህ የከፍታ ዘመን እየተሻገርን መሆኑን የምናውጅበት ነው ብለዋል። በሠንደቅ ዓላማ ቀን አከባበር ላይ የታደሙ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ቅድመ አያቶች የታመኑላት የአሁኑ ትውልድም ለመጪው የሚያስረክባት ደማቅ ዓርማ መሆኗን ገልጸዋል።   በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አራሬ ሞሲሳ፤ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ቅድመ አያቶች በደምና አጥንታቸው ጠብቀው ያቆዩት የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ዓርማ ምልክት ነው ብለዋል። የአሁኑ ትውልድም ድህነትን ድል በመንሳት ለመጪው ትውልድ ዕድገትና ብልጽግናን ማውረስ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠላቸው ግዙፍ ፕሮክቶችም ዘመን ተሻጋሪ የሉዓላዊነት መገለጫና የኩራት ምንጭ በመሆናቸው የዘንድሮውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አወቀ አምዛ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ቅድመ አያቶች የሀገርን ሉዓላዊ ነፃነትና ክብር በማስጠበቅ ለትውልድ ያሻገሯት ዓርማ ናት ብለዋል።   ሌላኛዋ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ከድጃ ሐሺም፤ የሠንደቅ ዓላማ ክብረ በዓል ታሪካችን የምናስታውስበት ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ የምንተጋበት ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ አዲስ የትብብር እና የወዳጅነት ምዕራፍ
Oct 13, 2025 121
የአፍሪካ ቀንድ ለበርካታ አስርት ዓመታት በዕድሎችና ፈተናዎች መንታ መንገድ ላይ የቆመ ቀጣና ነው። የቀጣናው ሰፊ ዕድሎች በግጭት፣ በስጋት ተጋላጭነት እና በአለመተማመን ሲሸፈኑ ይታያል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በጋራ የትብብር መንፈስ ለጋራ ብልጽግና እያደረጉት ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደአዲስ እየጎለበት መጥቷል። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ስትራቴጂካዊ አካባቢ ሲሆን ከኤደን ባህረ ሰላጤ እስከ ታላቁ ስምጥ ሸለቆ ከ160 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መኖሪያም ነው። ቀጣናው ሰፊ የተፈጥሮ ሀብቶችና ለም የግብርና መሬት የታደለ እንዲሁም አፍሪካን ከመካከለኛው ምስራቅ ብሎም ከሌሎች ጋር የሚያስተሳስሩ የውሃ ኮሪደሮች ያሉበት ነው። በቀጣናው ከትጥቅ ትግሎች እና ሽብርተኝነት የሚመነጩ የደህንነት ስጋቶች፣ ህገ-ወጥ ዝውውር፣ በተደጋጋሚ የሚከሰቱ ድርቆች፣ መፈናቀሎች፣ የምግብ ዋስትና አለመረጋገጥ፣ የአየር ንብረት ለውጥና ሌሎችም የቀጣናውን ሀገራት አይበገሬነትና አቅም እየፈተኑት ይገኛሉ። በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ጫናዎችና በየጊዜው የሚቀያየሩ የኃይል አሰላለፎች በቀጣናው የሚታዩ ፈተናዎችን የበለጠ አክብደውታል። የአፍሪካ ቀንድ ከውስጣዊ ትብብር ይልቅ የውጭ አካላት ፍላጎታቸውን ለማሳካት የሚራኮቱበት ቀጣና በሚል የሚፈርጁትም አሉ። አሁን አሁን በቀጣናው ከሚስተዋሉ ችግሮች ለየት ያለ አዲስ ነገር መታየትም መሰማትም እየጀመረ መጥቷል። በቀጣናው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቀየር ትብብርና ትስስር፣ ለመከባበርና የሰላም መንገድን ለመከተል ያሉ ፍላጎቶች እያደጉ መጥተዋል። ቀጣናዊ ትስስር የሚለው አጀንዳ ተገቢው ትኩረት እየተሰጠው መሆኑም እየተስተዋለ ይገኛል። የቀጣናው ሀገራት ወደ ውስጣቸው በመመልከት ፈተናዎችን በስክነት የመፍታት መንገድን መከተል ጀምረዋል። ለአፍሪካ ፈተናዎች አፍሪካዊ መፍትሄዎች የሚለውን መርህ ሀገራት እየገዙት ያለ አህጉራዊ ማዕቀፍ እና እሳቤ ሆኗል።   ለመሰረተ ልማት፣ ለኢነርጂ ትስስሮችና ለድንበር ተሻጋሪ ንግድ እየፈሰሰ ያለው መዋዕለ ንዋይ ቀጣናው የበለጠ እንዲተሳሰር መልካም አጋጣሚ ፈጥረዋል። ኢትዮጵያ በቅርቡ ያስመረቀችው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናዊ ትብብርና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰድ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለቀጣናው ገበያዎች አዳዲስ እድሎችን ይዞ መጥቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የዲፕሎማሲ ሁነቶች ሀገራት ለውይይት ያላቸውን ዝግጁነት የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲም ቅድሚያ ለጎረቤት የሚሰጥ ነው። ከቀጣናው ሀገራት ጋር በጋራ መልማትና ማደግ አበይት የፖሊሲው ምሰሶ ሆኖ በግልጽ ተቀምጧል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛው የሥራ ዘመን የ2018 የጋራ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር መንግስት በውጭ ጉዳይ ፖሊሲው ቅድሚያ ለጎረቤት የሚለውን መርህ አጠናክሮ እንደሚቀል ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት ከጎረቤት ሀገራት ጋር ዘርፈ ብዙ ትብብር ለመፍጠር ጥረት መደረጉንና ከጎረቤት ሀገራት ጋር ግጭት እንዳይፈጠር ጥረቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን አውስተዋል። ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች መከናወነቸውን ጠቅሰው በቀጣይነትም ኢኮኖሚያዊ ትብብርን የሚያጎለብቱ የመሰረተ ልማት ዝርጋታና የንግድ ልውውጥ እንዲጠናከሩ ይደረጋል ብለዋል። በዚህ ረገድ መንግስት የጀመራቸውን ትብብሮች አጠናክሮ እንደሚቀጭልና በአካባቢያችን ሰላምን ለማረጋገጥ አለመግባባቶችን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት አበክሮ እንደሚሰራም ነው ፕሬዚዳንቱ የገለጹት።   በቀጣናው እየተቀየረ ባለው ምህዳር ውስጥ የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ትብብር በቅርቡ ከታዩ መልካም የዲፕሎማሲ ጉዳዮች መካከል የሚጠቀስ ነው። ሁለቱ ሀገራት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የጋራ ፍላጎትና የጋራ ብልጽግናን መሰረት ባደረገ መልኩ ትብብራቸውን ለማጠናከር እየሰሩ ይገኛሉ። የሶማሊያ ፌደራል ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ትናንት ጥቅምት 2/2018ዓም በኢትዮጵያ ጉብኝት ማድረጋቸውና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ይታወሳል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ውይይት በቅርብ ጊዜ በሀገራቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት መካከል የተደረጉ ውይይቶች ቀጣይ አካል ሆኖ ሊወሰድ የሚችል ሲሆን በታህሣሥ 2017 ዓ.ም ላይ በቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን አሸማጋይነት የተደረገው የአንካራ ስምምነት በኢትዮጵያና ሶማሊያ መካከል ተፈጥሮ የነበረውን አለመግባባት የቀረፈ ስምምነት ነበር። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ሰላምና ትብብርን የሚያጎለብት፣ የሀገራቱን ሕዝቦች ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክር፣ ለቀጣናው ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና የሚበጅ ታሪካዊ ስምምነት እንደነበርም ይታወሳል። የአንካራ ስምምነት ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታገኝ ለምታደርገው ጥረት በር ከፋች ሆኗል። በዚህም የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት መሻት ዓለም አቀፍ ዕውቅና እንዲያገኝም አስችሏል። በዚህም የኢትዮጵያ የባህር በር የመሻት ጥያቄ ህጋዊ፣ ሞራላዊና ፖለቲካዊ መሰረት ያለው ነው። ይህም ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ የዘርፉ ምሁራንም ስምምነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር ለወዳጅ ሀገራት ጭምር ተስፋ የፈነጠቀ ክስተት ነው ሲሉም ገልጸውታል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ሶማሊያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው የገለጹት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማሊያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ አረጋግጠዋል። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለሀገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር መስጠታቸውም ይታወሳል። ሶማሊያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም ማረጋገጣቸው እንዲሁ። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደርጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረው ነበር። ከስምምነቱ በኋላ በሁለቱ ሀገራት መሪዎች መካከል የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ በጥር ወር 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያን መጎብኘታቸው ይታወሳል። ሀሰን ሼክ ማሃሙድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር መወያየታቸውና የጋራ መግለጫ ማውጣቸው አይዘነጋም። በውይይቱ ሁለቱ ሀገራት በየሀገራቱ ያላቸው ሙሉ የዲፕሎማሲ ውክልና በመመለስ ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ነበረበት ለመመለስ እና ለማሻሻል ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። የሀገራቱ መሪዎች የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖቻቸው በባለብዝሃ ወገንና በቀጣናዊ ፎረሞች ላይ የሀገራቱ የጋራ ፍላጎቶች ላይ በቅርበት መስራት እንዳለባቸውም አጽንኦት መስጠታቸው ይታወሳል። መሪዎቹ ለቀጣናው መረጋጋት የሁለቱ ሀገራት በጋራ መተማመንና መከባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ትብብር እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሻሻል፣ የጋራ መግባባት ለመፍጠርና የጋራ ግቦችን እውን ለማድረግ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። በተጨማሪም በውይይቱ ላይ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የጸጥታና ደህንነት ትብብራቸውን ለማጠናከር ቀጣይነት ያለው ስራ ማከናወን እንደሚያስፈልግም ተመላከቷል። በየጊዜው እያደገ የመጣውና አሳሳቢ የሆነው የታጠቁ ቡድኖች በቀጣናው ላይ የደቀኑት ስጋት በውይይቱ መነሳቱም ይታወሳል። በተጨማሪም መሪዎቹ ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት እና ንግድ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር መስራት እንዳለባቸውም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጠንካራ የኢኮኖሚ ትብብር በመፍጠር የንግድ ትስስራቸውን የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት መስመሮችን ለማስፋት እና የጋራ ብልጽግናቸውን ለማረጋገጥ ከስምምነት ላይ መድረሳቸው በጋራ መግለጫው ላይ ተጠቅሷል። መሪዎቹ ለአንካራው ስምምነት ትግበራ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸው ስምምነቱ ከሀገራቱ የወዳጅነት እና የአጋርነት መንፈስ የመነጨ እንደሆነም ተወስቷል። በስምምነቱ የተቀመጠውን የቴክኒክ ድርድሮች በፍጥነት እንዲጀመሩ ለማድረግ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን በጋራ መግለጫው መመላከቱም እንዲሁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የልዑካን ቡድናቸው በየካቲት ወር 2017 ሶማሊያን መጎብኘታቸው የሚታወስ ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) በሶማሊያ ያደረጉትን ጉብኝት አስመልክቶ በወቅቱ በሰጡት ማብራሪያ ጉብኝቱ የሁለቱን ጎረቤት ሀገራት ትብብርና ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው እንደሆነ አንስተው ነበር። ጉብኝቱ ሀገራቱ ወደ አዲስ የትብብር እና የወዳጅነት ምዕራፍ እንደደረሱ የሚያመላክት መሆኑን ጠቁመው ቀደም ብሎ በተለያየ ደረጃ ሲደረጉ የነበሩ ውይይቶችና ጉብኝቶች የሀገራቱን ትብብር ይበልጥ መጠናከሩን የሚያሳዩ በተለይም በፀጥታው ዘርፍ እና በሰላም ማስከበር ኢትዮጵያ ያላትን ተሳትፎና የሀገራቱን ትብብር መልክ ያስያዙ መናቸውንም እንዲሁ። የመሪዎቹ የጉብኝት ልውውጦች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸው እንዲሻሻል የሰጡትን ትኩረትና ያላቸውን የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም ተናግረው ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት፥ በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለፉት ጥቂት ወራት የነበራቸውን ገንቢ ውይይቶች ተከትሎ የመጣ እና የሀገራቱን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ነበረበት የመመለስን ስራ የሚያጠናክር መሆኑን የሀገራቱ መንግስታት የጋራ አቋም መግለጫ አመልክቷል። የሁለቱ መሪዎች የሀገራቱን የጋራ ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መልኩ ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሀገራቱ ህዝቦች ጥልቅ የሆነ ታሪካዊ ግንኙነትና የሚያስተሳስራቸው የጋራ ድንበር እንዳላቸው ያወሳው መግለጫው፥ በዚህ ረገድም በዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትብብር መተማመንን መገንባት ወሳኝ መሆኑ እንደታመነበትም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ለቀጣናዊ መረጋጋት እና ብልጽግናን እውን የማድረግ የጋራ ራዕይ ያላቸው ሀገራት መሆናቸውንም አመላክቷል። በዚህ ረገድ የሀገራቱ መሪዎች ዘላቂ ልማትን የሚያረጋግጡ፣ የኢኮኖሚ ትስስርን የሚያሳልጡና የህዝብ-ለህዝብ ትስስርን የሚያጠናክሩ ስትራቴጂካዊ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለመተግበር ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ነው መግለጫው ያመለከተው። በተጨማሪም መሪዎቹ በአንካራ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ የቴክኒክ ውይይት መጀመሩ መልካም የሚባል መሆኑንና ይህም ሀገራቱ ገንቢ ውይይትና ትብብር ለመፍጠር ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል። መሪዎቹ በሶማሊያ ብሔራዊ ወታደራዊ ኃይል እና በኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አዛዦች መካከል የደህንነት ትብብር ለማጠናከር ብሎም ቀጣናዊ መረጋጋትን ለማስፈን ለደረሱበት የጋራ መግባባት እውቅና ሰጥተዋል። ሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎታቸውን በማራመድ፣ ሰላም እና ደህንነትን በማረጋገጥ እንዲሁም የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ በማጠናከር ዜጎቻቸውን አልፈውም የአፍሪካ ቀንድን ተጠቃሚ ለማድረግ በጋራ እንደሚሰሩ መግለጻቸውም በመግለጫው ተንጸባርቋል። የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ መሃሙድ በጳጉሜን ወር 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ በነበራቸው ጉብኝት በቀጣናችን ፀጥታ እና መረጋጋት ብሎም ልማትን ለማረጋገጥ ያለንን ፅኑ አቋም በድጋሜ አረጋግጠናል ሲሉ በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መልካም ጉርብትና ትስስር ማደግ ለሀገራቱ መጻኢ ጊዜ አጋርነት መሰረትን የሚጥል በጎ ጅማሮ ነው። ከሀገራቱ ባለፈ ለአፍሪካ ቀንድ መልካምና ተስፋ ሰጪ ብስራት ነው ማለት ይቻላል። የሁለቱ ሀገራት የዲፕሎማሲ፣ ኢኮኖሚያዊና የደህንነት ትብብር ማደግ ለቀጣናው መረጋጋት፣ ንግድ ትስስር መጠናከር እና የጋራ እድገትን የሚያሳልጥ ነው። የሀገራቱ ትስስር መጠናከር እንደ መልካም የዲፕሎማሲ እርምጃ የሚታይ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት፣ አንድነት እና የኢኮኖሚ እድገትን ለማረጋገጥ ስትራቴጂካዊ እድል ይዞ መጥቷል። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ በቅርቡ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ ያደረጉት ንግግርም ይህንኑ ሀሳብ የሚያጠናክር ነው። በዚህ ወቅትም የግድቡ ተገንብቶ መመረቅ ለቀጣናው ኩራት መሆኑን ማንሳታቸው ይታወሳል። የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ ኢትዮጵያ እየሄደችበት ላለው የብልጽግና ጉዞ ወሳኝ መሆኑንና ፕሮጀክቱ ከአንድ ግድብነት ያለፈ መሆኑንም ተናግረዋል። በንግግራቸውም የሶማሊያ ፍላጎት በትብብር መልማትና ማደግ መሆኑን አሳውቀዋል። ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ያከናወነችው ሥራ ትልቅ ታሪክ መሆኑን በመግለጽ፤ ለሀገራቸው የሚጠቅም ተነሳሽነት መሆኑንም ነው ያስረዱት። የትብብሩ እድገት ለመሰረተ ልማት ትብብር፣ ለድንበር ተሻጋሪ የንግድ ልውውጥና የደህንነት ስጋቶች እንዲሁም አየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ ለጋራ ፈተናዎች በተቀናጀ መልኩ ምላሽ ለመስጠት በር ይከፍታል። የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለአፍሪካ እና ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ትስስር ግቦች መሳካት ትልቅ ድርሻ ይወጣል።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ጉዞ ዓለም በሚያየውና በሚመሰክረው ሀገራዊ ስኬት የተደገፈ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Oct 13, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየው፣ በሚዳስሰውና በሚመሰክርላቸው ስኬቶች የተደገፈ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ። 18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ’’ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነትና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል።   በዚሁ ወቅት ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፤ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ፍቅር፣ ክብርና ቃል ኪዳን በልባቸው የሚያድሱበት የጋራ ማንነታቸውን የሚያጎለብቱበትና የነገ ተስፋን የሚያጸኑበት ነው ብለዋል። ክብረ በዓሉ ያለፈውን የጀግንነት ገድል፣ የዛሬውን የልማት ጥረት፣ የነገውን የዕድገትና ብልጽግና ትልም በማጣመር ፈጣን ዕድገት ለምታስመዘግበው ኢትዮጵያ ድል አብሳሪና የጉዞ ህያው ምስክር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን የህልውና ፈተናዎች በህዝቦቿ የአንድነት ብርቱ ክንድ በጽናት ተሻግራ የራሷን ዕድል የመወሰን ብቃት እያስመሰከረች መሆኗንም አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየውና በሚዳስሰው ብሎም በሚመሰክርላቸው ሀገራዊ ስኬቶች የተደገፈ ነው ብለዋል።   የዚህ ብስራት መቅረዝና ከፍታም የዘመናት ህልም የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ የሀገርንና ቀጣናዊ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪ የደም ስር ለመሆን መብቃቱን ገልጸዋል። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ከብርሃን ምንጭነት ባሻገር ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሲቆሙ ታላላቅ ሀገራዊ የልማት ገድሎችን ማስመዝገብ እንደሚቻል በተግባር የተረጋገጠበት የሉዓላዊነት ማህተም መሆኑን ተናግረዋል። በአረንጓዴ ዐሻራም በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች መትከሏን አስታውሰው፤ ይህም የኢትዮጵያን ገጽታ በመቀየርና ለዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ በማበርከት ዓለም አቀፍ ከበሬታና ሞገስ ያስገኘላት የልማት ገድል ነው ብለዋል።   የዕድገት ጉዟችን ቀጣይ ምዕራፍ የኢኮኖሚ ብርታትን ማረጋገጥ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታውም በግብርና ምርታማነት የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከውጭ ከሚገባ የማዳበሪ ጥገኝነት በማላቀቅ ሀገራዊ ኢኮኖሚን የሚያጠናክር ታላቅ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ጋዝ ሃብትን በመጠቀም ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለኃይል ምንጭነት እንዲውል የማድረግ ውጥንም በአዲስ የኃይል ምንጭ የኢኮኖሚ ዕድገትና ብልጽግና ጉዞን እንደሚያፋጥን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ለወጣቶች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩና የሀገርን የከፍታ ዘመን በማይናወጥ መሠረት ለማስቀመጥ እንደሚረዱ ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ውጤታማነት ለማስቀጠልም በልዩነት ውስጥ ያለን ወርቃማ ውበት በማክበር የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ዘላቂ ሰላም መሠረት እየጣለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የሚከበረው በጠንካራ አንድነትና በበለጸገ ኢኮኖሚ ላይ ማቆም ሲቻል እንደሆነም አስገንዝበዋል። ለዚህም ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ትብብር ላይ የተመሰረተ ፍትሐዊ የባሕር በር የማግኘትና የመጠቀም መብታችን በሰላማዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና በሰጥቶ መቀበል መርህ ማስከበራችን ይቀጥላል ብለዋል። ኢትዮጵያውያንም በአዕምሯቸው ሰላምን በማጽናት በልባቸው የተስፋ ወጋገን አጥብቆ በመያዝ በክንዳቸው ብርታትም ሠንደቅ ዓላማና ሀገራቸውን መጠበቅ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።
የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ ይገባል
Oct 13, 2025 61
አርባ ምንጭ፣ዲላ፣ ቦንጋ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ) :- የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንደሚገባ ተመላከተ። 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሐሳብ በቦንጋ፣ ዲላና አርባ ምንጭ ከተሞች በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል። በቦንጋ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ላይ መልእክት ያስተላለፉት የካፋ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ግርማ ደፋር የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ስናከብር በየዘመኑ ለሀገር ነፃነትና ክብር የተከፈለውን ዋጋ በማሰብ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር ሉዓላዊነትና የነፃነት ምልክት መሆኑን ጠቅሰው ክብሩን በሚመጥን የስራ ትጋት በርትቶ በመስራት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገር ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ሰነድ ያቀረቡት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ንጉሴ ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው ለሰንደቅ ዓላማ ከፍታ የተከፈለው ዋጋ የማይረሳና በየዘመኑ እየተዘከረ የሚኖር መሆኑን ገልፀዋል። የቀኑ መከበር ሀገራዊ እሴቶችን አጠናክሮ ለትውልድ በማስተላለፍ አንድነታችንንና ህብረታችንን በማጠናከር ህብረ-ብሔራዊነትን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፣ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ምልክትና የሉዓላዊነት መገለጫ መሆኑን አንስተው ቀኑ ከሌሎች በዓላት በተለየ መልኩ በሰፊው መከበር እንዳለበት አንስተዋል። በአርባ ምንጭ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወላይቴ ቢቶ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር መለያ፣ የሉዓላዊነትና የአንድነታችን መገለጫ ነው ብለዋል፡፡ የሃገሪቱን የማንሠራራት ጉዞ ለማስቀጠልም ሁሉም በተሰማራበት መስክ ሰንደቅ ዓላማን ከፍ የሚያደርግ ተግባር መፈጸም እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ በተመሳሳይም በዲላ ከተማ በዓሉ ሲከበር የጌዴኦ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ምስጋና ዋቃዮ እንዳሉት ቀኑ ህገ መንግስታዊ መሰረት ያለውና ህብረተሰቡን በቅንነት ለማገልገል ዳግም ቃላችንን የምናድስበት ነው። የህብረ ብሔራዊትንና ሉዓላዊነት መገለጫ የሆነውን ሰንደቅ ዓላማ ማክበርና ማጉላት እንደሚገባም አመልክተዋል። ሰንደቅ ዓላማ የሃገራችን ኩራትና ነጻነት በመሆኑ የሚገባውን ክብር ልንሰጠው ይገባል ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጠቅ ዶሪ በተሰማራንበት ዘርፍ ውጤታማ በመሆን የሰንደቅ ዓላማ ክብርን ማጎልበት እንደሚገባም አንስተዋል።  
ሠንደቅ ዓላማችንን በክብር ለትውልድ ለማስተላለፍ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት ተግተን መስራት አለብን - ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)
Oct 13, 2025 61
ቦንጋ/ወላይታ ሶዶ/ወልቂጤ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፡- ሠንደቅ ዓላማችንን በክብር ለትውልድ ለማስተላለፍ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት ተግተን መስራት አለብን ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። 18ኛው የሠንደቅ ዓላም ቀን በቦንጋ፣ በወላይታ ሶዶና ወልቂጤ ከተሞች በድምቀት ተከብሯል። በቦንጋ በተከበረው በዓል ላይ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ፤ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረ ሰቦችና ሕዝቦች ህብር መገለጫ የሆነውን ሠንደቅ ዓላማን በክብር መጠበቅ እንደሚገባ ተናግረዋል።   በቀደምት አያቶቻችን አኩሪ ገድል ተጠብቆ የቆየውን ሠንደቅ ዓላማችንን በክብር ለትውልድ ለማስተላለፍ በሕብረ ብሔራዊ አንድነት ተግተን መሠራት አለብን ብለዋል። የቀኑ መከበር ለሠንደቅ ዓላማ መስዋእትነት የከፈሉ ጀግኖችን ለማሠብና ለትውልዱ ለማስተላለፍ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የገለጹት ደግሞ የካፋ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ግርማ ደፋር ናቸው። ሁሉም ዜጋ በተሠማራበት መስክ ሕዝቡን በታማኝነትና በቅንነት ለማገልገል በየዓመቱ ቃሉን የሚያድስበት መሆኑንም አመልክተዋል። ሠንደቅ ዓላማ ክብርና መለያችን ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ፖሊስ አባል ኮማንደር በድሩ ማሞ ናቸው። ቀደምት አያቶቻችን በክብር ያስረከቡንን ሠንደቅ ዓላማ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ተግተን እንሠራለን ብለዋል። በተመሳሳይ በዓሉ በወላይታ ሶዶ በተከበረበት ወቅት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ፤ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ጀግኖች አያቶች የሀገርን ነፃነት ያስከበሩበት ምልክት መሆኑን ተናግረዋል። የዘንድሮው የሠንደቅ ዓላማ ቀን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተመረቀበት እንዲሁም ሌሎች ታላላቅ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅት መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው አውስተው፤ ይህም የስኬቶቻችን ከፍታ ማሳያ ነው ብለዋል።   በርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተመስገን ጌታቸው፤ ሠንደቅ ዓላማ የኢትዮጵያዊነት መገለጫ ነው ብለዋል። ሁላችንም በየተሠማራንበት ጠንክረን በመስራት የህዳሴ ግድብን እንዳሳካን ሁሉ ሌሎችንም የጋራ ፕሮጀክቶች በመፈፀም ደምቀን ለመታየት ትጋታችንን አጠናከረን መቀጠል አለብን ሲሉ ተናግረዋል። በርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት የስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ዳይሬክተር አሠለፈች መብራቱ ፤ ሠንደቅ ዓላማ ከኢትዮጵያዊያን አልፎ ለሌሎች አፍሪካዊያንም የከፍታ ዘመን ማሳያ ዓርማ ነው ብለዋል። ይህንን ደግሞ ህዝቡን በታማኝነትና በሐቀኝነት በማገልገል እንዲሁም በሁሉም ዘርፎች መልካም አስተዳደርን በማስፈን የሠንደቅ ዓላማን ክብር በተግባር ለመግለጽ እየሠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በዓሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተከበረበት ወቅት የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ መነቴ ሙንዲኖ ፤ ጀግኖች አያቶቻችን የነፃነት ምልክት የሆነውን ሠንደቅ ዓላማ ለአዲሱ ትውልድ ማስረከባቸውን ተናግረዋል። ትውልዱም አብሮነቱንና ሀገራዊ አንድነቱን በማጠናከርና ልማትን በማፋጠን ኢትዮጵያን ከፍ የማድረግ አደራውን ማጠናከር አለበት ብለዋል።
የግብጽ የእኔ ብቻ ልጠቀም ባይነት ዘመን አክትሟል፤ በናይል ወንዝ አጠቃቀም አዲስ የትብብር ምዕራፍ ተከፍቷል
Oct 13, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፡- የግብጽ የእኔ ብቻ ልጠቀም ባይነት ዘመን አብቅቶ በናይል ወንዝ ላይ በጋራ የመልማት አዲስ የትብብር ምዕራፍ ተከፍቷል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ግብጽ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና የአባይ ወንዝ ዙሪያ የምታደርጋቸውን ጠብ አጫሪ ንግግሮች በጽኑ አውግዟል። ግብጽ በቅኝ ግዛት ዘመን ውሎች የብቸኛ ተጠቃሚነት አባዜ መጠመዷን እንደቀጠለችበት አመልክቷል። የግብጽ ከፍተኛ ባለስልጣን ሀገራቸው በናይል ተፋሰስ ሀገራት በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ የውሃ ጉድጓድ መቆፈሪያ እና የዝናብ መሰበብሰቢያ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ አነስተኛ ይዞታ ያላቸውን ፕሮጀክቶችን በመገንባት ከአፍሪካ ጋር አጋርነቷን እያሳየች ነው ማለታቸው እውነተኛ የቀጣናዊ ትብብር ፍላጎት ማሳያ አለመሆኑንም ገልጿል። እውነተኛ የአፍሪካ አጋርነት በውሃ ሀብቶች ፍትሃዊነት እና እኩልነትን በመጠቀም ማመንና የሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት የመልማት መብትን እውቅና መስጠትን የሚጠይቅ መሆኑንም ሚኒስቴሩ በመግለጫው አመላክቷል። ግብጽ በናይል ወንዝ ጊዜው ያለፈበትን የታሪካዊ መብቶች እሳቤ የሙጥኝ ብላ መቀጣሏን ገልጾ፤ ይህም ዓለም አቀፍ ህግን ያላከበረና የተፋሰሱን ሀገራት ህጋዊ መብቶች ከግምት ውስጥ ያላስገባ መሆኑን አብራርቷል። የኢትዮጵያ መንግስት የናይል ወንዝ የመልማት መብቷን በመጠቀም እያደገ የመጣውን የኢነርጂ እና የውሃ ፍላጎቶቿን ለመመለስ እያከናወነች ያለውን ስራ በየትኛውም አይነት ጫና እንደማታቆምና አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታውቋል። ሚኒስቴሩ በመግለጫው ግብጽ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እና የናይል ቤዚን የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ላይ ስታደርጋቸው የነበሩ ድርድሮች ታማኝነት የጎደላቸው እንደነበሩም ገልጿል። የናይል ቤዚን የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት በተፋሰሱ ሀገራት መካከል ብቸኛ የጋራ የውሃ ተጠቃሚነት ማዕቀፍ መሆኑንም አስረድቷል። ኢትዮጵያ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሁሌም ዝግጁ መሆኗንም ገልጿል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የመልማት መብት እና ቀጣናዊ ትብብር መገለጫ መሆኑንም ሚኒስቴሩ በመግለጫው አስታውቋል። ማስፈራሪያዎችንና ከመሰረታዊ የትብብር እሳቤዎች ያፈነገጡ አካሄዶችን በማቆም ከሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት ጋር በጋራ መከባበር እና ፍትሃዊ መርሆዎች አብሮ መስራት እንደሚገባ አመላክቷል። ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ዘላቂ አጠቃቀም ላይ ከተፋሰሱ አገራት ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኗንም ነው ሚኒስቴሩ በመግለጫው ያረጋገጠው።
ሰንደቅ ዓላማ የሀገር አንድነት ማስጠበቂያ ብሔራዊ ዓርማ ነው
Oct 13, 2025 91
አምቦ/ ነቀምቴ ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፡- ሰንደቅ ዓላማ የአገር አንድነት ማስጠበቂያ ብሔራዊ ዓርማና የነጻነታችን ምልክት ነው ሲሉ የሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ የስራ አመራሮች እና ሰራተኞች ተናገሩ። 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የኢንዱስትሪው ሰራተኞችና አመራሮች በተገኙበት ተከብሯል። በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኮሎኔል ስለሺ ነገራ፣ ሰንደቅ ዓላማ የነጻነት ምልክት ነው ብለዋል። የሰንደቅ ዓላማ ቀን ስናከብር ለሀገር አንድነት እና ሉዓላዊነት ዋጋ የከፈሉትን በማሰብ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ነጻነት ምልክት መሆኑን ገልጸዋል። የዛሬው ትውልድም የቀደምት አያቶች ፈለግ ተከትሎ የሀገር ሉዓላዊነት እና አንድነትን ለማስጠበቅ ከፊት መሰለፍ አለበት ሲሉም ተናግረዋል። ከበዓሉ ተሳታፊዎች ሌተናል ኮሎኔል ጌቱ ብርሃኑ በበኩላቸው ሰንደቅ ዓላማ የሀገር አንድነት ማስጠበቂያ ብሔራዊ አርማ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ቀደምት ጀግኖች አባቶች ሀገርን በክብር ያወረሱን ለሰንደቅ ዓላማ ባላቸው ፍቅር መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬው ትውልድም ለዚህ በጎ ዓላማ መቆም አለበት ብለዋል። ሀምሳ አለቃ አዲሱ ጉዲና፣ ለሰንደቅ ዓላማ ክብር እና ለሀገር ሉዓላዊነት የሚጠበቅባቸውን መሰዋእትነት ለመክፈል ምንጊዜም ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ምክትል አስር አለቃ ላቀች ሙሉዓለም ወታደር በጀግንነት ወጥቶ ለሀገሩ ዳር ድንበር መስዋትነት የሚከፍለው ለሰንደቅ ዓላማ በመታመኑ እንደሆነ ጠቅሰው፤ ለስንደቅ ዓላማ ክብር ሁሉም ዘብ መቆም አለበት ነው ያሉት። በተመሳሳይ በነቀምቴ ከተማ የሰንደቅ ዓላማ ቀን አካባበር ላይ የተገኙት የነቀምቴ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መሰረት ታደሰ እንደተናገሩት ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር መገለጫ ነው ብለዋል። የሀገርን ክብር እና ሉዓላዊነት ለማስከበር ቀደምት አባቶች ብዙ ዋጋ ከፍለዋል ያሉት አፈ ጉባኤዋ አሁን ያለው ትውልድም በልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ሀገር ወዳድነቱን ማረጋገጥ አለበት ብለዋል። የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ ተወካይ ረዳት ፕሮፌሰር መላኩ ጌታሁን በበኩላቸው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ስናከብር ሀገራችን የጀመረችውን የልማት ስራዎች በመደገፍ ለውጤታማነቱ በመረባረብ መሆን አለበት ሲሉ ገልጸዋል።  
ሠንደቅ ዓላማ መላው ኢትዮጵያውያንን ለጋራ ዓላማ የሚያሰባስብ ዓርማ ነው
Oct 13, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ሠንደቅ ዓላማችን መላው ኢትዮጵያውያንን ለጋራ ዓላማ የሚያሰባስብ የማንነት መገለጫ ዓርማ ነው ሲሉ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ ገለጹ። አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ 18ኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን "ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ" በሚል መሪ ሐሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል፡፡   በዚሁ ወቅት የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ሀገርን ከወራሪዎች ለመከላከልና ነጻነትን ለማስጠበቅ ሲደረግ የነበረው ተጋድሎ ምልክት መሆኑን አስገንዝበዋል። የመረጃና ደኅንነት ተቋሙ አባላትም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ ሉዓላዊነትና ክብር ለማስጠበቅ በሚያደርጉት ስምሪት የሠንደቅ ዓላማውን ትልቅ አደራ በልባቸው በመያዝ በከፍተኛ የሀገር ፍቅር መንፈስ እስከ መስዋዕትነት ድረስ ዋጋ ይከፍላሉ ብለዋል፡፡   ሠንደቅ ዓላማው መላው ኢትዮጵያውያንን ለጋራ ዓላማ የሚያሰባስብ የማንነት መገለጫ ዓርማ ነው ማለታቸውን አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመላክቷል። ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተወጣጡትና በኅብረ-ብሔራዊ ስብጥር ለአንድ ሀገራዊ ዓላማ የተሰለፉት የተቋሙ አባላትም፤ በሠንደቅ ዓላማው ጥላ ስር ሀገራዊ ደኅንነትን የማረጋገጥ ተልዕኮን በላቀ መንፈስ የሚወጡ መሆኑን አስታውቀዋል። በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በተከበረው 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ተሳትፈዋል።
የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት ሀገር የመገንባት አቅም የሚጎለብትበት የማንሠራራት ጉዞ ዓርማ ነው - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Oct 13, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ፈተናዎችን በጽናት በመሻገር አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት ሀገር የመገንባት አቅም የሚጎለብትበት የማንሰራራት ጉዞ ዓርማ መሆኑን የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን ’’ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነትና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል።   የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በዚሁ ወቅት፤ በሕገ መንግስቱና በሠንደቅ ዓላማ አዋጅ ድንጋጌ መሠረት የሠንደቅ ዓላማ ቀን በጥቅምት ወር መጀመሪያ ሳምንት ሰኞ በየዓመቱ ይከበራል ብለዋል። የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ የዜጎች የብዝሃነት፣ የእኩልነትና የሕብረብሔራዊ አንድነት መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል። የሠንደቅ ዓላማ ቀንም ለሠንደቅ ዓላማችን ልንሰጠው የሚገባውን ክብር የምናድስበት፣ ቃልኪዳናችንን የምናጸናበትና ብሔራዊ የአርበኝነታችንን የምንቀሰቅስበት ነው ብለዋል።   ለሠንደቅ ዓላማ ቀን የተሰጠው መሪ ሀሳብም የዛሬውን ተግባር፣ የነገውን ምኞትና ትልም በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማም የውስጥና የውጭ ጠላቶች ሊሰብሩት የማይችሉት የሕብረብሔራዊ አንድነትና የሉዓላዊነት ምሽግ መሆኑን አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ፈተናዎችን በጽናት በመሻገር አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት ሀገር የመገንባት አቅም የሚጎለብትበትና ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚታይበት የማንሰራራት ጎዞ ዓርማ መሆኑን አንስተዋል። ሠንደቅ ዓላማችን በታሪክ ውጣ ውረዶች ውስጥ የጽናታችን ምልክት ነው ያሉት አፈጉባኤ ታገሠ፤ ዛሬም በዘላቂ ልማትና ብልጽግና ወደ ብሩህ የከፍታ ዘመን እየተሻገርን መሆኑን የምናውጅበት ነው ብለዋል። በሠንደቅ ዓላማ ቀን አከባበር ላይ የታደሙ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ቅድመ አያቶች የታመኑላት የአሁኑ ትውልድም ለመጪው የሚያስረክባት ደማቅ ዓርማ መሆኗን ገልጸዋል።   በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አራሬ ሞሲሳ፤ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ቅድመ አያቶች በደምና አጥንታቸው ጠብቀው ያቆዩት የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ዓርማ ምልክት ነው ብለዋል። የአሁኑ ትውልድም ድህነትን ድል በመንሳት ለመጪው ትውልድ ዕድገትና ብልጽግናን ማውረስ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል። የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠላቸው ግዙፍ ፕሮክቶችም ዘመን ተሻጋሪ የሉዓላዊነት መገለጫና የኩራት ምንጭ በመሆናቸው የዘንድሮውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አወቀ አምዛ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ቅድመ አያቶች የሀገርን ሉዓላዊ ነፃነትና ክብር በማስጠበቅ ለትውልድ ያሻገሯት ዓርማ ናት ብለዋል።   ሌላኛዋ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ከድጃ ሐሺም፤ የሠንደቅ ዓላማ ክብረ በዓል ታሪካችን የምናስታውስበት ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ የምንተጋበት ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ አዲስ የትብብር እና የወዳጅነት ምዕራፍ
Oct 13, 2025 121
የአፍሪካ ቀንድ ለበርካታ አስርት ዓመታት በዕድሎችና ፈተናዎች መንታ መንገድ ላይ የቆመ ቀጣና ነው። የቀጣናው ሰፊ ዕድሎች በግጭት፣ በስጋት ተጋላጭነት እና በአለመተማመን ሲሸፈኑ ይታያል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በጋራ የትብብር መንፈስ ለጋራ ብልጽግና እያደረጉት ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደአዲስ እየጎለበት መጥቷል። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ስትራቴጂካዊ አካባቢ ሲሆን ከኤደን ባህረ ሰላጤ እስከ ታላቁ ስምጥ ሸለቆ ከ160 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መኖሪያም ነው። ቀጣናው ሰፊ የተፈጥሮ ሀብቶችና ለም የግብርና መሬት የታደለ እንዲሁም አፍሪካን ከመካከለኛው ምስራቅ ብሎም ከሌሎች ጋር የሚያስተሳስሩ የውሃ ኮሪደሮች ያሉበት ነው። በቀጣናው ከትጥቅ ትግሎች እና ሽብርተኝነት የሚመነጩ የደህንነት ስጋቶች፣ ህገ-ወጥ ዝውውር፣ በተደጋጋሚ የሚከሰቱ ድርቆች፣ መፈናቀሎች፣ የምግብ ዋስትና አለመረጋገጥ፣ የአየር ንብረት ለውጥና ሌሎችም የቀጣናውን ሀገራት አይበገሬነትና አቅም እየፈተኑት ይገኛሉ። በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ጫናዎችና በየጊዜው የሚቀያየሩ የኃይል አሰላለፎች በቀጣናው የሚታዩ ፈተናዎችን የበለጠ አክብደውታል። የአፍሪካ ቀንድ ከውስጣዊ ትብብር ይልቅ የውጭ አካላት ፍላጎታቸውን ለማሳካት የሚራኮቱበት ቀጣና በሚል የሚፈርጁትም አሉ። አሁን አሁን በቀጣናው ከሚስተዋሉ ችግሮች ለየት ያለ አዲስ ነገር መታየትም መሰማትም እየጀመረ መጥቷል። በቀጣናው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቀየር ትብብርና ትስስር፣ ለመከባበርና የሰላም መንገድን ለመከተል ያሉ ፍላጎቶች እያደጉ መጥተዋል። ቀጣናዊ ትስስር የሚለው አጀንዳ ተገቢው ትኩረት እየተሰጠው መሆኑም እየተስተዋለ ይገኛል። የቀጣናው ሀገራት ወደ ውስጣቸው በመመልከት ፈተናዎችን በስክነት የመፍታት መንገድን መከተል ጀምረዋል። ለአፍሪካ ፈተናዎች አፍሪካዊ መፍትሄዎች የሚለውን መርህ ሀገራት እየገዙት ያለ አህጉራዊ ማዕቀፍ እና እሳቤ ሆኗል።   ለመሰረተ ልማት፣ ለኢነርጂ ትስስሮችና ለድንበር ተሻጋሪ ንግድ እየፈሰሰ ያለው መዋዕለ ንዋይ ቀጣናው የበለጠ እንዲተሳሰር መልካም አጋጣሚ ፈጥረዋል። ኢትዮጵያ በቅርቡ ያስመረቀችው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናዊ ትብብርና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰድ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለቀጣናው ገበያዎች አዳዲስ እድሎችን ይዞ መጥቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የዲፕሎማሲ ሁነቶች ሀገራት ለውይይት ያላቸውን ዝግጁነት የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲም ቅድሚያ ለጎረቤት የሚሰጥ ነው። ከቀጣናው ሀገራት ጋር በጋራ መልማትና ማደግ አበይት የፖሊሲው ምሰሶ ሆኖ በግልጽ ተቀምጧል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛው የሥራ ዘመን የ2018 የጋራ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር መንግስት በውጭ ጉዳይ ፖሊሲው ቅድሚያ ለጎረቤት የሚለውን መርህ አጠናክሮ እንደሚቀል ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት ከጎረቤት ሀገራት ጋር ዘርፈ ብዙ ትብብር ለመፍጠር ጥረት መደረጉንና ከጎረቤት ሀገራት ጋር ግጭት እንዳይፈጠር ጥረቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን አውስተዋል። ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች መከናወነቸውን ጠቅሰው በቀጣይነትም ኢኮኖሚያዊ ትብብርን የሚያጎለብቱ የመሰረተ ልማት ዝርጋታና የንግድ ልውውጥ እንዲጠናከሩ ይደረጋል ብለዋል። በዚህ ረገድ መንግስት የጀመራቸውን ትብብሮች አጠናክሮ እንደሚቀጭልና በአካባቢያችን ሰላምን ለማረጋገጥ አለመግባባቶችን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት አበክሮ እንደሚሰራም ነው ፕሬዚዳንቱ የገለጹት።   በቀጣናው እየተቀየረ ባለው ምህዳር ውስጥ የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ትብብር በቅርቡ ከታዩ መልካም የዲፕሎማሲ ጉዳዮች መካከል የሚጠቀስ ነው። ሁለቱ ሀገራት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የጋራ ፍላጎትና የጋራ ብልጽግናን መሰረት ባደረገ መልኩ ትብብራቸውን ለማጠናከር እየሰሩ ይገኛሉ። የሶማሊያ ፌደራል ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ትናንት ጥቅምት 2/2018ዓም በኢትዮጵያ ጉብኝት ማድረጋቸውና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ይታወሳል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ውይይት በቅርብ ጊዜ በሀገራቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት መካከል የተደረጉ ውይይቶች ቀጣይ አካል ሆኖ ሊወሰድ የሚችል ሲሆን በታህሣሥ 2017 ዓ.ም ላይ በቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን አሸማጋይነት የተደረገው የአንካራ ስምምነት በኢትዮጵያና ሶማሊያ መካከል ተፈጥሮ የነበረውን አለመግባባት የቀረፈ ስምምነት ነበር። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ሰላምና ትብብርን የሚያጎለብት፣ የሀገራቱን ሕዝቦች ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክር፣ ለቀጣናው ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና የሚበጅ ታሪካዊ ስምምነት እንደነበርም ይታወሳል። የአንካራ ስምምነት ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታገኝ ለምታደርገው ጥረት በር ከፋች ሆኗል። በዚህም የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት መሻት ዓለም አቀፍ ዕውቅና እንዲያገኝም አስችሏል። በዚህም የኢትዮጵያ የባህር በር የመሻት ጥያቄ ህጋዊ፣ ሞራላዊና ፖለቲካዊ መሰረት ያለው ነው። ይህም ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ የዘርፉ ምሁራንም ስምምነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር ለወዳጅ ሀገራት ጭምር ተስፋ የፈነጠቀ ክስተት ነው ሲሉም ገልጸውታል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ሶማሊያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው የገለጹት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማሊያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ አረጋግጠዋል። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለሀገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር መስጠታቸውም ይታወሳል። ሶማሊያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም ማረጋገጣቸው እንዲሁ። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደርጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረው ነበር። ከስምምነቱ በኋላ በሁለቱ ሀገራት መሪዎች መካከል የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ በጥር ወር 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያን መጎብኘታቸው ይታወሳል። ሀሰን ሼክ ማሃሙድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር መወያየታቸውና የጋራ መግለጫ ማውጣቸው አይዘነጋም። በውይይቱ ሁለቱ ሀገራት በየሀገራቱ ያላቸው ሙሉ የዲፕሎማሲ ውክልና በመመለስ ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ነበረበት ለመመለስ እና ለማሻሻል ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። የሀገራቱ መሪዎች የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖቻቸው በባለብዝሃ ወገንና በቀጣናዊ ፎረሞች ላይ የሀገራቱ የጋራ ፍላጎቶች ላይ በቅርበት መስራት እንዳለባቸውም አጽንኦት መስጠታቸው ይታወሳል። መሪዎቹ ለቀጣናው መረጋጋት የሁለቱ ሀገራት በጋራ መተማመንና መከባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ትብብር እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሻሻል፣ የጋራ መግባባት ለመፍጠርና የጋራ ግቦችን እውን ለማድረግ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። በተጨማሪም በውይይቱ ላይ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የጸጥታና ደህንነት ትብብራቸውን ለማጠናከር ቀጣይነት ያለው ስራ ማከናወን እንደሚያስፈልግም ተመላከቷል። በየጊዜው እያደገ የመጣውና አሳሳቢ የሆነው የታጠቁ ቡድኖች በቀጣናው ላይ የደቀኑት ስጋት በውይይቱ መነሳቱም ይታወሳል። በተጨማሪም መሪዎቹ ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት እና ንግድ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር መስራት እንዳለባቸውም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጠንካራ የኢኮኖሚ ትብብር በመፍጠር የንግድ ትስስራቸውን የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት መስመሮችን ለማስፋት እና የጋራ ብልጽግናቸውን ለማረጋገጥ ከስምምነት ላይ መድረሳቸው በጋራ መግለጫው ላይ ተጠቅሷል። መሪዎቹ ለአንካራው ስምምነት ትግበራ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸው ስምምነቱ ከሀገራቱ የወዳጅነት እና የአጋርነት መንፈስ የመነጨ እንደሆነም ተወስቷል። በስምምነቱ የተቀመጠውን የቴክኒክ ድርድሮች በፍጥነት እንዲጀመሩ ለማድረግ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን በጋራ መግለጫው መመላከቱም እንዲሁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የልዑካን ቡድናቸው በየካቲት ወር 2017 ሶማሊያን መጎብኘታቸው የሚታወስ ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) በሶማሊያ ያደረጉትን ጉብኝት አስመልክቶ በወቅቱ በሰጡት ማብራሪያ ጉብኝቱ የሁለቱን ጎረቤት ሀገራት ትብብርና ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው እንደሆነ አንስተው ነበር። ጉብኝቱ ሀገራቱ ወደ አዲስ የትብብር እና የወዳጅነት ምዕራፍ እንደደረሱ የሚያመላክት መሆኑን ጠቁመው ቀደም ብሎ በተለያየ ደረጃ ሲደረጉ የነበሩ ውይይቶችና ጉብኝቶች የሀገራቱን ትብብር ይበልጥ መጠናከሩን የሚያሳዩ በተለይም በፀጥታው ዘርፍ እና በሰላም ማስከበር ኢትዮጵያ ያላትን ተሳትፎና የሀገራቱን ትብብር መልክ ያስያዙ መናቸውንም እንዲሁ። የመሪዎቹ የጉብኝት ልውውጦች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸው እንዲሻሻል የሰጡትን ትኩረትና ያላቸውን የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም ተናግረው ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት፥ በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለፉት ጥቂት ወራት የነበራቸውን ገንቢ ውይይቶች ተከትሎ የመጣ እና የሀገራቱን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ነበረበት የመመለስን ስራ የሚያጠናክር መሆኑን የሀገራቱ መንግስታት የጋራ አቋም መግለጫ አመልክቷል። የሁለቱ መሪዎች የሀገራቱን የጋራ ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መልኩ ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሀገራቱ ህዝቦች ጥልቅ የሆነ ታሪካዊ ግንኙነትና የሚያስተሳስራቸው የጋራ ድንበር እንዳላቸው ያወሳው መግለጫው፥ በዚህ ረገድም በዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትብብር መተማመንን መገንባት ወሳኝ መሆኑ እንደታመነበትም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ለቀጣናዊ መረጋጋት እና ብልጽግናን እውን የማድረግ የጋራ ራዕይ ያላቸው ሀገራት መሆናቸውንም አመላክቷል። በዚህ ረገድ የሀገራቱ መሪዎች ዘላቂ ልማትን የሚያረጋግጡ፣ የኢኮኖሚ ትስስርን የሚያሳልጡና የህዝብ-ለህዝብ ትስስርን የሚያጠናክሩ ስትራቴጂካዊ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለመተግበር ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ነው መግለጫው ያመለከተው። በተጨማሪም መሪዎቹ በአንካራ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ የቴክኒክ ውይይት መጀመሩ መልካም የሚባል መሆኑንና ይህም ሀገራቱ ገንቢ ውይይትና ትብብር ለመፍጠር ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል። መሪዎቹ በሶማሊያ ብሔራዊ ወታደራዊ ኃይል እና በኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አዛዦች መካከል የደህንነት ትብብር ለማጠናከር ብሎም ቀጣናዊ መረጋጋትን ለማስፈን ለደረሱበት የጋራ መግባባት እውቅና ሰጥተዋል። ሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎታቸውን በማራመድ፣ ሰላም እና ደህንነትን በማረጋገጥ እንዲሁም የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ በማጠናከር ዜጎቻቸውን አልፈውም የአፍሪካ ቀንድን ተጠቃሚ ለማድረግ በጋራ እንደሚሰሩ መግለጻቸውም በመግለጫው ተንጸባርቋል። የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ መሃሙድ በጳጉሜን ወር 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ በነበራቸው ጉብኝት በቀጣናችን ፀጥታ እና መረጋጋት ብሎም ልማትን ለማረጋገጥ ያለንን ፅኑ አቋም በድጋሜ አረጋግጠናል ሲሉ በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መልካም ጉርብትና ትስስር ማደግ ለሀገራቱ መጻኢ ጊዜ አጋርነት መሰረትን የሚጥል በጎ ጅማሮ ነው። ከሀገራቱ ባለፈ ለአፍሪካ ቀንድ መልካምና ተስፋ ሰጪ ብስራት ነው ማለት ይቻላል። የሁለቱ ሀገራት የዲፕሎማሲ፣ ኢኮኖሚያዊና የደህንነት ትብብር ማደግ ለቀጣናው መረጋጋት፣ ንግድ ትስስር መጠናከር እና የጋራ እድገትን የሚያሳልጥ ነው። የሀገራቱ ትስስር መጠናከር እንደ መልካም የዲፕሎማሲ እርምጃ የሚታይ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት፣ አንድነት እና የኢኮኖሚ እድገትን ለማረጋገጥ ስትራቴጂካዊ እድል ይዞ መጥቷል። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ በቅርቡ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ ያደረጉት ንግግርም ይህንኑ ሀሳብ የሚያጠናክር ነው። በዚህ ወቅትም የግድቡ ተገንብቶ መመረቅ ለቀጣናው ኩራት መሆኑን ማንሳታቸው ይታወሳል። የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ ኢትዮጵያ እየሄደችበት ላለው የብልጽግና ጉዞ ወሳኝ መሆኑንና ፕሮጀክቱ ከአንድ ግድብነት ያለፈ መሆኑንም ተናግረዋል። በንግግራቸውም የሶማሊያ ፍላጎት በትብብር መልማትና ማደግ መሆኑን አሳውቀዋል። ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ያከናወነችው ሥራ ትልቅ ታሪክ መሆኑን በመግለጽ፤ ለሀገራቸው የሚጠቅም ተነሳሽነት መሆኑንም ነው ያስረዱት። የትብብሩ እድገት ለመሰረተ ልማት ትብብር፣ ለድንበር ተሻጋሪ የንግድ ልውውጥና የደህንነት ስጋቶች እንዲሁም አየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ ለጋራ ፈተናዎች በተቀናጀ መልኩ ምላሽ ለመስጠት በር ይከፍታል። የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለአፍሪካ እና ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ትስስር ግቦች መሳካት ትልቅ ድርሻ ይወጣል።
ማህበራዊ
በአማራ ክልል ግልጽና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ችሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተጀመረው ተግባር ይጠናከራል-የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት
Oct 13, 2025 56
ባህር ዳር፤ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)-በአማራ ክልል ግልጽና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ችሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተጀመረው ተግባር ተጠናከሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ። በክልሉ በክረምት የዳኞች የእረፍት ጊዜ ምክንያት ዝግ ሁኖ የቆየው የችሎት አገልግሎት ዛሬ ተጀምሯል። በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ አደራ በችሎት አገልግሎት ማስጀመሪያ ሥነ ስርአት ላይ እንደገለጹት፣ ከክልል እስከ ወረዳ ባሉ ፍርድ ቤቶች መደበኛ የችሎት አገልግልት ዛሬ መሰጠት ተጀምሯል።   በፍርድ ቤቶች የሚሰጠው መደበኛ የችሎት ተግባር ቀልጣፋ እንዲሆን ባለፈው ዓመት በዲጂታል የታገዘ የችሎት ሥራ መጀመሩን ጠቁመው፤ አገልግሎቱም የተገልጋዩን ገንዘብ፣ ወጪና እንግልት ይቀንሳል ብለዋል። በዲጂታል የታገዘ የችሎት ሥራን በማስፋፋት የተገልጋይን ጊዜ፣ ወጪና ገንዘብ ለመቀነስ የተጀመረው ተግባር በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክረምት ወቅት በተካሄደ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ የዲጂታል ችሎትን በተሟላ መልኩ ለማስኬድ የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውንም አውስተዋል። ባለፈው በጀት ዓመት የእድሳት ሥራ የተከናወነለት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሕንጻ የዳኝነት ስርዓቱን ቀልጣፋና ጊዜውን የሚመጥን ለማድረግ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አቶ ሀብታሙ አስገንዝበዋል። ዲጂታል አሰራሩ ባለጉዳዮች ዞን በሚገኙ ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ሆነው ወደክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሳይመጡ ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት የሚያገኙበት ስርአት ለመዘርጋት መቻሉንም ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪ ህብረተሰቡ ነጻ፣ግልጽና ተአማኒነት ያለው ፍትህ አግኝቶ እርካታን ለመፍጠር እንደሚያስችል አስረድተዋል።      
በምስራቅ ቦረና ዞን በክልላዊና ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ሽልማትና እውቅና ተሰጠ
Oct 13, 2025 44
ነገሌ ቦረና ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- በምስራቅ ቦረና ዞን በ2017 ትምህርት ዘመን በክልላዊና ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ሽልማትና እውቅና ተሰጠ ። በአገር አቀፍ ፈተናው የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ አስተዋጾ ላደረጉ መምህራንና ትምህርት ቤቶችም ሽልማትና እውቅና ተሰጥቷል፡፡ የምስራቅ ቦረና ዞን ትምህርት ጽህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ ዮናስ በሪሶ በስነ ስርአቱ ላይ እንዳሉት በዞኑ በ12 ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ 573 ነጥብ ተመዝግቧል፡፡ በመምህራን አቅም ግንባታ፣ በትምህርት ቤቶች ደረጃ ማሻሻል፣ በዲጂታል ቤተመጻህትና በትምህርት አቀራረብ ዘዴ መሻሻል ላይ በትኩረት መሰራቱ ለውጤቱ መመዝገብ ከፍተኛ አስተዋጾ ማድረጉን አመልክተዋል፡፡ በዞኑ ለብሄራዊ ፈተና ከተቀመጡ ተማሪዎች ውስጥ 108ቱ የከፍተኛ ትምህርት የመግቢያ ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡት መካከል 76ቱ የነገሌ ቦረና ከተማ ኢፋ ቦሩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ናቸው ብለዋል፡፡ የምስራቅ ቦረና ዞን አስተዳደር ተወካይ አቶ መሀመድ ኑራ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ለ6ኛ፣ ለ8ኛና ለ12 ክፍል 14 ተማሪዎች የገንዘብ ሽልማትና ሜዳሊያ መሰጠቱን ተናግረዋል። አቶ ዮናስ አክለውም ለውጤቱ እገዛ ያደረጉ ስምንት መምህራን፣ ሰባት ትምህርት ቤቶችና አንድ ወረዳ አስተዳደር የዋንጫ ሽልማትና የእውቅና ምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡ የዞኑ አስተዳደር ህዝቡን በማስተባበር የትምህርት ስብራትን ለመጠገንና ጥራቱንም ለማሻሻል እየተሰራ ነው ብለዋል። በትምህርት ስራው ግንባር ቀደም በመሆን ሜዳሊያ ተሸላሚ ከሆኑት መምህራን መካከል መምህር እውነቱ ማሞ የእውቅና ሽልማቱ የበለጠ ለመስራት እንዳነሳሳቸው ተናግረዋል። በቀጣይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ጠንክረው እንደሚሰሩ አመላክተዋል። ከተሸላሚ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ገልገሎ ጉፋ የሜዳሊያና የገንብ ሽልማቱ በቀጣይም ጠንክሮ በማጥናት ከፍተኛ ውጤት ለማምጣት ብርታት እንደሆነለት ገልፅዋል።    
የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን ቀድሞ መከላከልና በራስ አቅም ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የተቀናጀ አቅም እየተገነባ ነው
Oct 13, 2025 72
ሰመራ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን ቀድሞ መከላከልና በራስ አቅም ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የተቀናጀ አቅም እየተገነባ መሆኑን የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሸነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) ገለጹ። ዓለም አቀፍ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ቀን "ለአደጋ ስጋት አይበገሬነት ግንባታ ትኩረት እንስጥ" በሚል መሪ ሃሳብ በአፋር ክልል በሰመራ ከተማ ተከብሯል።   በሁነቱ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሸነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር)፤ አደጋዎችን ለመከላከልና በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት በሁሉም ረገድ ዝግጁ መሆን ይገባል ብለዋል። በተለይም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ምጣኔ ሃብት መገንባት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።   በተፈጥሮ የሚመጡ አደጋዎችን ቀድሞ የመከላከልና በራስ አቅም ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የተቀናጀ አቅም መፍጠር እንደሚገባ አንስተው ለዚህም ዘላቂና የተቀናጀ አሰራር መፍጠር ያስፈልጋል ነው ያሉት። በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ፤ በተለይም የግብርና ልማት ስራዎችን በማስፋትና ምርታማነትን በማሳደግ ለአደጋዎች ጥንቃቄና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባት እንደሚገባ ገልጸዋል። የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ሀገራዊ የኢኮኖሚ አቅምን በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ማረጋገጥ የጋራ አጀንዳ ሆኖ በተጠናከረ መልኩ መቀጠል አንዳለበትም አስገንዝበዋል።   በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የአፋር ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኀላፊ አሊ መሐመድ፤ በክልሉ የሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ቀድሞ የመከላከልና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅም ለመፍጠር እየተሰራ ነው ብለዋል። የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ የአደጋ ተጋላጭነትን የመቀነስ ስትራቴጂና ምርታማነትን የማሳደግ ስራም እንዲሁ። በመርሃ ግብሩ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ(ዶ/ር)፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የአደጋ ስጋት አመራሮች ተሳትፈዋል።
ብሔራዊ የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኅብረብሄራዊ አንድነት እንዲጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Oct 13, 2025 66
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ ብሔራዊ የወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኅብረብሄራዊ አንድነት እንዲጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሙና አህመድ ገለጹ። ሚኒስትር ዴኤታዋ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ብሔራዊ በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ መስኮች የኀብረተሰቡን ተጠቃሚነት ከፍ ያደረጉ ውጤቶች እየተገኘበት ነው። በአቅመ ደካሞች ቤት እድሳትና ግንባታ፣ የጤና ምርመራና ህክምና፣ በትራፊክ አገልግሎት፣ በማዕድ ማጋራትና ሌሎች ዘርፎች በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ለውጡን ተከትሎ ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተሰጠው ትኩረት ትልልቅ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን ጠቅሰው በኀብረተሰቡ ዘንድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ባህል እየሆነ መምጣቱንም አንስተዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከኢኮኖሚ ጠቀሜታዎች ባሻገር የእርስ በእርስ ትስስር እንዲጎለብት አወንታዊ ሚና እየተጫወተ ነውም ብለዋል። በተለይም ብሔራዊ የወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኅብረብሄራዊ አንድነት እንዲጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አንዱ የሌላውን እሴት እና ባህል እንዲያውቅ በማድረግ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጠናከር በማድረግ በኩል የላቀ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ዘላቂ ለማድረግ በአሰራር የማስደገፍ ሥራ በትኩረት እየተከናዋነ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ደኤታዋ ብሄራዊ የበጎ ፈቃድ ፖሊሲን ሥራ ላይ ለማዋል እየተሰራ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል። ፖሊሲው አስፈላጊው ግበዓት ከተሟላለት በኋላ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ሥራ ላይ እንደሚውልም አብራርተዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ውጤታማነት ለማሳደግ በቴክኖሎጂ በታገዘ አሠራር የማስደገፍ ጉዳይ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አመልክተዋል። በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጠቀሜታዎች ባለፈ ለጥቅል ሀገራዊ ምርት ያለውን አስተዋጽኦ መለካት የሚያስችል መስፈርት እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልጸዋል። መስፈርቱን ለማዘጋጀት የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮዎች ተቀምሮ በግብዓትነት መወሰዱን ጠቁመው በዘርፉ የተሻለ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ዓይነተኛ ሚና እንዳለውም አስረድተዋል።
ኢኮኖሚ
በክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው - አቶ አብርሃም ማርሻሎ
Oct 13, 2025 65
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለፁ። የክልሉ የሥራና ክህሎት ቢሮ ባካሄደው የሴክተር ጉባኤ አቶ አብርሃም እንደገለጹት በክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጎልበት የዜጎች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።   ‎በዚህም በተለይ ወጣቶች ተወዳዳሪ በመሆንና የተሻለ ሀብት በመፍጠር ረገድ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ነው የገለጹት። ‎የአካባቢን የልማት አቅም በመለየትና ወጣቶችን በቂ ክህሎት በማስጨበጥ እሴት በሚጨምሩ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው ተጠቃሚ የሚሆኑበት መደላድል የመፍጠር ሥራው በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በጉባኤው የተገኙት ሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በበኩላቸው እንዳሉት እንደ ሀገር ብቁ የሰው ኃይል በማፍራትና ዘላቂና አስተማማኝ የሥራ ዕድል በመፍጠር ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።   ክህሎት መር በሆነ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ እንዲሁም በተቋም ግንባታ ላይ የሪፎርም አጀንዳዎችን በመቅረጽ የተለያዩ ሥራዎች እተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። በዚህም ላለፉት ተከታታይ አራት ዓመታት በአማካይ በዓመት 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር እንደተቻለ ጠቅሰው፣ በቀጣይም ይህን ለማጠናከር ትኩረት ተደርጓል ብለዋል። በሲዳማ ክልል ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት የሚበረታታ መሆኑን ጠቅሰው የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የሲዳማ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረፅዮን አበበ ከ2015 ዓ.ም በፊት የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው ክህሎትን ዋንኛ ትኩረት ያደረገ ባለመሆኑ በዘርፉ የሚፈለገው ውጤት ሳይመዘገብ ቆይቷል።   ባለፉት ሁለት ዓመታት አንድም ዜጋ ያለ በቂ ክህሎትና ሥልጠና ወደሥራ እንዳይገባ አቅጣጫ ተቀምጦ ሲሰራ መቆየቱንም አመልክተዋል፡፡ ይህም ቀደም ሲል የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ላይ ይስተዋል የነበረው የውጤት ማጣት፣ የመበተን፣ የመሰላቸት እና ሀብት መፍጠር ያለመቻል ችግር ተፈትቶ ውጤት መታየት መጀመሩን ገልጸዋል። እንደ ቢሮ ኃላፊዋ ገለፃ በ2017 በጀት ዓመት በመደበኛ ሥልጠና ከ30 ሺህ በላይ እንዲሁም በአጫጭርና ገበያ ተኮር ሥልጠናዎች ከ61 ሺህ በላይ ዜጎችን ማሰልጠን ተችሏል ፡፡ በሥልጠና ተቋማት፣ በአገልግሎት መስጫ እና በሥራ ማዕከላት ላይ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥርዐትን በመዘርጋትም ዘርፉን የማዘመን ሥራም ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። በመድረኩ በተያዘው ዓመት በዘርፉ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ባለፈው በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና አጋር አካላት የዕውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል፡፡  
በ90 ቀናት ውስጥ እያደገ የመጣውን የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ የሚመልሱ ተግባራት ተከናውነዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Oct 13, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 90 ቀናት ውስጥ እያደገ የመጣውን የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ የሚመልሱ ተግባራት መከናወናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ሦስተኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ተካሂዷል። የምክር ቤቱ አባላት በተመረጡባቸው አካባቢዎች ከመራጮቻቸው ጋር ባደረጉት ውይይት የተነሱ ጥያቄዎችንና አስተያያቶችን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ አቅርበዋል።   በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ለከተማዋ ነዋሪዎች ተስፋ የሰጡ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ የመዲናዋ የኮሪደር ልማት አዲስ አበባን ልዩና ማራኪ ገጽታ እንዳላበሳት ተናግረዋል። ህብረተሰቡ አዳጊ የሆኑ ጥያቄዎች እንዳሉት ገልጸው፤ በትራንስፖርት እንዲሁም በውሀ አቅርቦት ላይ ያሉ እጥረቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ምን እንደታሰበ የምክር ቤቱ አባላት ጠይቀዋል። የዋጋ ንረትን እንዲሁም የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ምን ይመስላሉ ሲሉም አንስተዋል። ከአገልግሎት አሰጣጥ አኳያም የሚስተዋሉ ውስንነቶችን ለማቃለል ከተማ አስተዳደሩ እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎች እንዲብራሩላቸው ጥያቄ አቅርበዋል። በስራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም ሴቶች እና ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች ትግበራ ላይም እየተከናወኑ ባሉ ስራዎች ዙሪያ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት ዘጠና ቀናት ከ96ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል። ኢንተርፕራይዞች ለመንግስት የልማት ስራዎችና ለኢንዱስትሪዎች የጥሬ እቃ እንዲያቀርቡ በማድረግ የሁለት ቢሊዮን ብር የገበያ ትስስር መፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡ በዓመቱ መጨረሻም ለ350ሺህ ወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀምበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በቅርቡ ተመርቆ ወደ ስራ የገባው አዲስ የመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት የዚህ ማሳያ መሆኑን ገልጸው፤ አገልግሎቱን በሁሉም ክፍለ ከተሞች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ሀገራዊና ከተማ አቀፍ የተለያዩ ሃይማኖታዊና ህዝባዊ በዓላት በስኬት ማጠናቀቅ መቻሉን ያነሱት ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ ናቸው። ለዚህም የከተማዋ ነዋሪ፣ የፀጥታ መዋቅሩ እና የፖለቲካ አመራሩ የማይተካ ሚና መጫወታቸውን ተናግረዋል፡፡ የእነዚህ ድምር ውጤትም የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ከተማዋ የትኩረት ማዕከል እንድትሆን ማስቻሉን ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሰጡት ማጠቃለያ የምክር ቤት አባላት ያነሱት ጥያቄ የከተማዋ ህዝብ ዋና አጀንዳና ቅድሚያ የሚሰጠው ልማት መሆኑን ያሳያል። ጥያቄዎቹ የበለጠ መልማትን የተመለከቱ፣ በርካታ የስራ ዕድል መፍጠርን፣ ተጨማሪ ውጤቶችን ማስመዝገብና ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጡ ስራዎች በዘላቂነት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። ባለፉት 90 ቀናት ከከተማ ጀምሮ እስከ ወረዳ ከባለድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ ጋር የሚሰሩ ስራዎች በዕቅድ ተይዘው መከናወናቸውን አስረድተዋል። የአቅመ ደካማና ለሀገር ባለውለታዎች ቤቶችን መልሶ ግንባታና የኑሮ ውድነት ጫና መቀነስ የሚያስችሉ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውንም ገልጸዋል። በከተማዋ አገልግሎት ማዘመንና የስራ ዕድል ፈጠራ ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ተግባራት መካከል መሆናቸውን አንስተዋል። በ90 ቀናት ለማሳካት የታቀዱ ተግባራትን በሙሉ በስኬታማነት መፈጸም መቻሉን ነው ያስረዱት ከንቲባዋ። ለአብነትም በክረምት ወራት 2ሺ 500 የመኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት ታቅዶ የ3ሺህ 400 ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝና ከእነዚህ መካከልም ከ2ሺህ 500 በላይ የሚሆኑት ተጠናቀው ለህብረተሰቡ መተላለፋቸውን ገልፀዋል። የኑሮ ውድነት ጫናን ለመቀነስ በቅዳሜና እሁድ ገበያና በሁሉም አካባቢ እየተስፋፉ በሚገኙ የገበያ ማዕከላት ምርቶችን በስፋት በማቅረብ ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ነው ያብራሩት። በከተማዋ በርካታ ሁነቶች በስኬትና በድምቀት የተካሄዱት ህዝቡ ከመንግስትና ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት በመቻሉ መሆኑንም ተናግረዋል።
በባሕርዳር  እየተከናወኑ  የሚገኙ  አበረታች  የልማት ተግባራት የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት የሚያግዙ ናቸው
Oct 13, 2025 80
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- በባሕር ዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች የልማት ተግባራት እንደሀገር የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት የሚያግዙ መሆናቸው ተመላከተ። በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ የተመራ ቡድን በባሕርዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን ተዘዋውሮ ተመልክቷል።   በዚህ ወቅት ከንቲባው አለማየሁ አሰፋ ፤ ኮሪደርን ጨምሮ ደረጃቸውን የጠበቁ የመንገድ መሰረተ ልማቶችና ወደ ጣና የሚያስገቡ መንገዶች፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫና ሌሎችንም የግንባታ ተግባራት ተዘዋውረው መመልከታቸውን ተናግረዋል። በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ተግባራት ባሕር ዳርን ይበልጥ ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ እንድትሆን የሚያስችላት መሆኑን ገልጸዋል። የኮሪደር ልማቱን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር ጣናን ለጎብኚዎችና ለነዋሪዎች የመግለጥ ተግባር ከተማዋን ሳቢና ማራኪ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል። እየተገነቡ የሚገኙት የልማት ተግባራት የሕዝብ ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ እንደሆኑ መገንዘባቸውን ጠቁመው፤ ይህም ሀገሪቱ ወደ ብልፅግና ለመሸጋገር የጀመረችውን ጉዞ ለማፋጠን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች የልማት ተግባራት የተጀመረውን የማንሰራራት ጉዞ ለማሳካት የሚያግዙ ናቸው ብለዋል።   አመራሩ ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀናጅቶ የከተማዋን እድገት ለማፋጠን እየተጋ መሆኑን ማረጋገጣቸውን ያነሱት ከንቲባው፤ ከባሕርዳር ያገኙትን ልምድና ተሞክሮ በቢሾፍቱ በሚገኙ የኃይቅ ዳርቻዎች ተግባራዊ በማድረግ የከተማቸውን ዕድገት ለማፋጠን እንደሚሰሩ አስታውቀዋል። የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ የባሕር ዳር ከተማን ዕድገት የሚያፋጥኑ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   የከተማዋን ሰላም በማፅናት የኮሪደር ልማት፣ የስማርት ሲቲ፣ ሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ የአረንጓዴና ሌሎች የልማት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል። በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አለማየሁ አሰፋ የተመራው ቡድን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን መመልከቱ የጋራ የልምድና ተሞክሮ ልውውጥ ለማድረግ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። በቀጣይም የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር አመራሮች ወደ ቢሾፍቱ ከተማ አቅንተው በመጎብኘት ግንኙነቱንና ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እንደሚሰሩም አመልክተዋል።
ሀገራዊ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ከፍ ባለ የሠንደቅ ዓላማ ክብርና ፍቅር እውን እንዲሆኑ ሙያዊ ሃላፊነታችንን እናጠናክራለን
Oct 13, 2025 170
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡-እንደ አገር የተያዙ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ከፍ ባለ የሠንደቅ ዓላማ ክብርና ፍቅር እውን እንዲሆኑ ሙያዊ ሃላፊነታቸውን እንደሚያጠናክሩ የኢዜአ አመራሮችና ሰራተኞች አረጋገጡ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች 18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን''ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት ለብሔራዊ አንድነታችን ሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ'' በሚል መሪ ሀሳብ በፓናል ውይይትና ሠንደቅ ዓላማ በመስቀል አክብረዋል።   አመራሮችና ሰራተኞቹ የሠንደቅ ዓላማ ቀንን ሲያከብሩ እንደ ሀገር የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ ከፍ ባለ የሰንደቅ ዓላማ ክብርና ፍቅር ሙያዊ ሃላፊነታቸውን በመወጣት መሆኑን አረጋግጠዋል። ሠንደቅ ዓላማ ኢትዮጵያውያን በየዘመኑ የገጠማቸውን ፈተናዎች በድል በማለፍ የሀገርን ዳር ድንበር ለማስጠበቅ የደም መስዋዕትነት ከፍለው ያስገኙት የነጻነት አርማ መሆኑም ተነስቷል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ፥ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለአፍሪካ ኩራት የሚሆኑ ግዙፍ አገራዊ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች ባለችበት ጊዜ የሠንደቅ ዓላማ ክብርና ፍቅር የበለጠ ይጎላል ብለዋል።   እንደ አገር የተጀመሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን አንድነትን የበለጠ በማጠናከር ከግብ ለማድረስ ቃላችንን ማደስ አለብን ነው ያሉት። እንደ አገር የተጀመሩ ግዙፍ የልማት ስራዎች ወደ ኋላ እንዳይቀለበሱ የጋራ ርብርብ ማድረግ ወሳኝ መሆኑንም ነው ያነሱት። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የክልል ዴስክ ምክትል ዋና አዘጋጅ በለጠ አድነው፥ እንደ አገር በቀጣይ የተያዙ ትላልቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ከፍ ባለ የሠንደቅ ዓላማ ክብርና ፍቅር ለመፈጸም ሙያዊ ሃላፊነታችንን በትጋት እንወጣለን ብሏል።   በተለይም ከአገራዊ ለውጡ በኋላ ኢትዮጵያውያን አንድነታቸውን የበለጠ በማጠናከር ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን እውን ማድረግ መቻላቸውን ያነሳው ደግሞ በኢዜአ የክልል ዴስክ ምክትል ዋና አዘጋጅ ሀብታሙ አክሊሉ ነው።   ይህም የአገርንና የሰንደቅ ዓላማን ክብር የበለጠ ከፍ የሚያደርግና በራስ የመፈጸም አቅምን ያሳየ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የክልል ግንኙነት ቡድን መሪ ዮሃንስ ወንድይራድ የውይይት መነሻ ሀሳብ ባቀረበበት ወቅት፥ ኢዜአ ብሄራዊ መግባባትና አገራዊ ገጽታ የመገንባት ተልዕኮውን በብቃት ለመወጣት የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ነጋሲ አምባዬ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ፥ ኢትዮጵያና ህዝቦቿ በቀደምት አባቶች ደማቅ ታሪክ የተጻፈ ሰንደቅ ዓላማ ባለቤት ናቸው ብለዋል።   ትውልዱ ይህን የአባቶቹን አኩሪ ታሪክ ጠብቆ የራሱን አሻራ ለማሳረፍ ያሉ ዕድሎችን አሟጦ መጠቀም ይገባዋል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ብሎም ለዓለም ኩራት የሆኑ አኩሪ ታሪኮች ያላት አገር እንደመሆኗ ይህን ታሪክ ጠብቆ ማቆየትና የሰንደቅ ዓላማን ክብር ከፍ ማድረግ የሁሉም ሃላፊነት መሆኑንም ነው ያነሱት።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ ኢኖቬተሮች እና ስራ ፈጣሪዎች እየተሳተፉበት የሚገኘው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ሁነት በዱባይ እየተካሄደ ነው
Oct 13, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- 45ኛው የገልፍ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) ዛሬ በዱባይ ዓለም አቀፍ የንግድ ማዕከል ተጀምሯል። “የዳታ ማዕከላት በነገ ዲጂታል መሰረተ ልማቶች ግንባታ ውስጥ ያላቸው ቁልፍ ሚና” የአውደ ርዕዩ መሪ ሀሳብ ነው። በዓለም ላይ ግዙፍ ከሚባሉት የቴክኖሎጂ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ጀማሪ ስራ ፈጠራ ትዕይንቶች አንዱ በሆነው ጂአይቴክስ ከ180 ሀገራት የተወጣጡ ከ6 ሺህ 500 በላይ አቅራቢዎች፣ 1 ሺህ 800 ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች እና 1 ሺህ 200 ባለሀብቶች ተሳታፊ ሆነዋል። ጂአይቴክስ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች፣ የመንግስት ተቋማት፣ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ኢኖቬተሮች እና ተመራማሪዎችን በአንድ መድረክ ያገናኘ ነው።   ዓለም አቀፍ አውደ ርዕዩ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት፣ የጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ኢኖቬሽን፣ የጤና እና ባዮ ቴክኖሎጂዎች፣ ኮሙኒኬሽን፣ ሮቦቲክስ፣ የቀጣዩ ትውልድ ቴክኖሎጂዎች፣ የኮምፒዩተር ስርዓቶች እና ማሽኖችን ጨምሮ በርካታ ዘርፎችን ይዟል። በጂአይቴክስ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች እና ባለሀብቶች እየተሳተፉ እንደሚገኙ Pulse of Africa ሚዲያ ከስፍራው ዘግቧል። እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው ዓለም አቀፍ ሁነት በዋናነት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ መሰረት ያደረጉ ፈጠራዎች እንደሚቀርቡና በዘርፉ ላይ ትኩረት ያደረጉ ውይይቶች እንደሚካሄዱም ተመላክቷል። እንደ ተባበሩት መንግስታት የንግድ እና ልማት ጉባዔ (አንክታድ) ጥናት ከሆነ እንደ አውሮፓውያኑ የዘመን ቀመር በ2033 የሰው ሰራሽ አስተውሎት ገበያ ወደ 4 ነጥብ 8 ትሪሊዮን የአሜሪካን ዶላር ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል። አሁን ላይ የ757 ነጥብ 58 ቢሊዮን ዶላር የገበያ ድርሻ እንዳለው ይገመታል። አንክታድ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቴክኖሎጂ ገበያው ያለው ድርሻ ወደ 29 በመቶ ማደጉን ጠቅሶ፤ ይህም ኤአይ በዘርፉ እያደገ የመጣውን ከፍተኛ አቅም የሚያመላክት ነው። ይህ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቀጣይ ጊዜያት በዓለም ላይ የሚኖረውን ተፅእኖ ያሳያል። የገልፍ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) እ.አ.አ 1981 አንስቶ እየተካሄደ የሚገኝ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ሁነት ነው።
በአፍሪካ ለወጣቶች ክህሎትና ቴክኖሎጂን በማስታጠቅ የፈጠራ አቅማቸውን ማሳደግ ይገባል
Oct 13, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ለወጣቶች ክህሎትና ቴክኖሎጂን በማስታጠቅ የፈጠራ አቅማቸውን ለማሳደግ በትብብር መሥራት እንደሚገባ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎት ሳምንት "የአፍሪካን የኢንዱስትሪ መፃኢ ዘመን ለማጎልበት፤ ክህሎት ለኢኖቬሽን፣ ዕድገትና ለዘላቂነት" በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት መካሄድ ጀምሯል።   የአፍሪካ ክህሎት ሳምንት ለኢንዱስትሪ ዕድገት ኢኖቬሽንና ክህሎትን ለማጠናከር፤ አካታችና ጥራት ያለው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናን ለማሳደግ፣ የግሉ ዘርፍና የመንግስትን ትብብር እና ቀጣናዊ ትስስርን ለማጎልበት እንዲሁም የአረንጓዴ ልማትና ቴክኖሎጂን ለማበረታታት ያስችላል ተብሏል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) በጉባኤው መክፈቻ ወቅት እንዳሉት፤ የክህሎት ሳምንት ለአፍሪካ ወሳኝና ስትራቴጂያዊ ጉዳይ ነው፡፡ አፍሪካ በአስቸጋሪና በብዙ ፈተናዎች ውስጥ መሆኗን ገልጸው፤ የወጣቶች ጉዳይ ከንግግር ባለፈ ፈጣን የተግባር ርምጃ የሚያስፈልገው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከአፍሪካ ህዝብ አበዛኛው ከ25 ዓመት በታች መሆኑ ትልቅ አቅም ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ነገር ግን ይሄ ኃይል በክህሎትና በቴክኖሎጂ እንዲዳብርና ለፈጠራ እንዲዘጋጅ ማድረግ ይገባል ነው ያሉት፡፡ በአፍሪካ ክህሎትና ፈጠራን በማሳደግ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ሽግግር ለማምጣት ወጣቶችን በቴክኖሎጂ ማስታጠቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ የአህጉሪቱን የኢንዱስትሪ ምርታማነት ለማሻሻል፣ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የወጣቶችን የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን አቅም ማጠናከር ከዛሬ መጀመር እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ ወጣቶች ቴክኖሎጂን የሚጠቀሙ ብቻ ሳይሆኑ የሚፈጥሩና ለገበያ የሚያቀርቡ እንዲሆኑ የክህሎት ልማት ልዩ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተውም፤ የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎችን ወደ ገበያ ዕድል መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ፈጠራ የታከለበት ታዳሽ ኃይልን ማስፋት፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባት፣ ቀጣይነት ያለው ግብርናን ማሳደግ፣ እንዲሁም ለወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ላይ ሊተኮር ይገባል ነው ያሉት፡፡ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ስርዓት ፍላጎትን መሰረት ማድረግ እንዳለበት ገልጸው፤ ወጣቶች አፍሪካን የሚገነቡ የፈጠራ ሀሳቦችን ማፍለቅ እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ ሥራ ፈጣሪዎችን ማበረታታትና በቴክኖሎጂ፣ በፖሊሲ እና በአሰራር መደገፍ እንዲሁም አፍሪካውያን መተባበርና የወጣቶች የሥራና የሙያ ነጻ እንቅስቃሴን መፍቀድ አለባቸው ብለዋል፡፡   በአፍሪካ ሕብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽን የትምህርት ክፍል ኃላፊ ሶፊያ አሽፓላ፤ ለአፍሪካ አካታች የኢንዲስትሪ አብዮትና የዲጂታል ሽግግር ዕድገት ቀልጣፋ የትምህርትና ስልጠና ሥርዓት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረት የወጣቶችን ተሳትፎና የዲጂታል ዕድገት ለማሳለጥ አሕጉራዊ የዲጂታል ሽግግርና ትምህርትና ስልጠና ስርዓት በመቅረጽ መሰረት መጣሉን ገልጸዋል፡፡ ይሄውም በአፍሪካ እውቀትና ኢኖቬሽን መር ማህበረሰብ ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለኢንዱስትሪ ኢኮኖሚና ማህበረሰብ ዕድገት ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን በማንሳት፤ የአፍሪካ ክህሎት ሳምንት የአጀንዳ 2063 እና ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡   የ"ሁሉም አፍሪካ ወጣቶች ማሕበር" አማካሪና "የጋራ እሴት" በጋና ማኔጂንግ ዳይሬክተር አንድሪውስ አኮቶ አዶ በበኩላቸው፤ መሪዎች የአፍሪካን ዕድገትና ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በጋራ አጀንዳዎችና መፍትሔዎች ላይ ብዙ ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ወጣቶችን የዕቅዶቻቸው ማዕከልና ግንባር ቀደም አድርገው መስራታቸውን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ለዜጎቿ ክህሎት ልማት የወሰደችው ርምጃ ለሌሎች አፍሪካውያን ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ዛሬ በአዲስ አበባ ይጀመራል
Oct 13, 2025 113
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፦ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ዛሬ በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ይሳተፉበታል። የአህጉሪቷን የክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር የሁነቱ አበይት ትኩረት ነው። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች የሚቀርቡበት መሆኑን ገልጿል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ ሲጠናቀቅ የአፍሪካ ክህሎት ልማትን አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቆያል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው::
ሀገርን የሚያሻግሩ ትልልቅ የዲጂታል ኢኒሼቲቮችን የሳይበር ደህንነት ማረጋገጥ ዋነኛ ትኩረት መሆን አለበት
Oct 11, 2025 184
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገርን የሚያሻግሩ ዲጂታል የልማትና የአገልግሎት ኢኒሼቲቮችን ለማሳካት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ ዋነኛ የትኩረት ማዕከል መሆን እንዳለበት የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለም ፀሐይ ጳውሎስ ገለፁ። ከዛሬ ጥቅምት 1 ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆየው ስድስተኛው አገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር የማስጀመሪያ መረሃ-ግብር በአዲስ አበባ ተካሒዷል።   የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምፀሐይ ጳውሎስ ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ስኬታማ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል። የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጅማሮ ማሳያ የሆኑ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የተመረቁና የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች መንግስት ለዘላቂ ልማትና እድገት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩ ናቸው ብለዋል። የዜጎችን የዕለት ተዕለት የህይወት እንቅስቃሴና የመንግሥትን አገልግሎት የሚያሳልጡ የዲጂታል አሠራሮችን በመተግበር ተጨባጭ ለውጦች መምጣታቸውን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅት ከ900 በላይ የሚሆኑና በተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ አማካይነት ለተገልጋዮች ተደራሽ እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ቴክኖሎጂና ልማት ተሰናስለው የሚሔዱ ናቸው ያሉት ሚኒስትሯ፤ የልማት ስራዎቹ ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲቆይ ማድረግ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል። የሳይበር ደህንነት ጉዳይ ከሀገር ሉዓላዊነት ጋር የሚተሳሰር በመሆኑ በዘርፉ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ለዚህም በተለያዩ አማራጮች ተደራሽ የሚደረጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ጉልህ ሚና እንዳላቸው ነው የጠቆሙት። የሳይበር ደህንነት ወር እንደ ሀገር በሳይበር ደህንነት ላይ የሚከናወኑ ተግባራትን በስፋት ለማስገንዘብ እድል የሚፈጥርና የተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር የሚያግዝ ነው ብለዋል።   ስለሆነም በመላ ሀገሪቱ በሳይበር ደህንነት ዙሪያ የሚከናወኑ ተግባራት ውጤታማ በሆነ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት በሀገሪቱ የተከናወኑ የልማት ስራዎች፣ ተገንብተው የተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችና የቴክኖሎጂ ውጤቶች የሀገሪቷን ኢኮኖሚያዊና ሁሉን አቀፍ እድገት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል።   እነዚህና ሌሎች የልማት ስራዎች ለዘላቂ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ እድገት ያላቸውን ፋይዳ ለማጉላት ደህንነታቸውን በአግባቡ ጠብቆ ማቆየት የግድ ያስፈልጋል ነው ያሉት። ለዚህም የሳይበር ደህንነት ጉዳይን ወጥነት ባለው መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ መንግስት በቁርጠኝነት እየሰራ ስለመሆኑ አንስተዋል። ለአብነትም በየዓመቱ የሚከበረው የሳይበር ደህንነት ወር የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብር አንዱና ዋነኛው መሆኑን አስረድተዋል። በእነዚህና ሌሎች የቅድመ መከላከል ስራዎች በተከናወኑ ተግባራት የሳይበር ጥቃት ምጣኔን መቀነስ ተችሏል ነው ያሉት። የዘንድሮው የሳይበር ደህንነት ወር "የሳይበር ደህንነት የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሔድ ይሆናል፡፡
ስፖርት
ኢትዮጵያ የዓለም ዋንጫ የመጨረሻ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዋን ከቡርኪናፋሶ ጋር ዛሬ ታደርጋለች
Oct 12, 2025 119
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ዛሬ ከቡርኪናፋሶ ጋር ትጫወታለች። የሀገራቱ ጨዋታ በኦገስት 4 ስታዲየም ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ይደረጋል። በምድብ አንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ በዘጠኝ ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በፊት ከጊኒ ቢሳው ጋር ባደረገው የማጣሪያ መርሃ ግብር 1 ለ 0 በማሸነፍ በምድቡ ሁለተኛ ድሉን ማስመዝገቡ ይታወቃል። በብራማ ትራኦሬ የሚሰለጥነው የቡርኪናፋሶ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በፊት ከሴራሊዮን ጋር ባደረገው ጨዋታ 1 ለ 0 አሸንፏል። ቡድኑ ነጥቡን ወደ 18 ከፍ በማድረግ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሁለቱ ሀገራት በዚሁ ምድብ ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ ቡርኪናፋሶ 3 ለ 0 ማሸነፏ የሚታወስ ነው። ሀገራቱ ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው አምስት የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ አንድ ጊዜ ስታሸንፍ ቡርኪናፋሶ ሶስት ጊዜ ድል ቀንቷታል። አንድ ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። በጨዋታዎቹ ቡርኪናፋሶ 12 ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ኢትዮጵያ ሶስት ግቦችን አስቆጥራለች። ከዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ ለሆነው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የዛሬው ጨዋታ የማጣሪያ ጉዞውን በድል ለመደምደም ያስችለዋል። ቡርኪናፋሶ ማሸነፍ ከቻለች ለዓለም ዋንጫው ለማለፍ በሚደረገው የጥሎ ማለፍ ውድድር ለመሳተፍ የሚያስችላትን እድል ታሰፋለች። በዚሁ ምድብ የምትገኘው ግብጽ በ23 ነጥብ ለዓለም ዋንጫ በቀጥታ ማለፏ የሚታወስ ነው። በምድብ አንድ ግብጽ ከጊኒ ቢሳው፣ ጅቡቲ ከሴራሊዮን ዛሬ በተመሳሳይ ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች ነው
Oct 13, 2025 61
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ገለጹ፡፡ በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስተባባሪነት በአረንጓዴ ትራንስፖርትና በታዳሽ ኃይል ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች የአዳማ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተጎብኝቷል፡፡ በጉብኝቱ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን፣ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰንን ጨምሮ ከኢትዮጵያ እና ኬንያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ ኩባንያዎች ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴዔታ በርኦ ሀሰን በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የትራንስፖርት ዘርፉን ጨምሮ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ ባከናወነቻቸው ተግባራት በርካታ ለውጦችን አስመዝግባለች ብለዋል፡፡ ለዚህም በሕዳሴ ግድብ፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብርና በንፋስ ኃይል ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች ትልቅ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዘርፉን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅና ከአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የጸዳ እንዲሆን ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል፡፡ መንግሥት ታዳሽ ኃይል የሚጠቀም የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍን እውን ለማድረግ ጠንካራ የፖሊሲ ድጋፍ ስለማድረጉ አንስተዋል። በዚህም በርካታ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በማንሳት፥ ባለሀብቶችም በዘርፉ ኢንቨስት እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና መንግስት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓት የተሰማሩ ተቋማትን እንደሚያበረታታ አረጋግጠዋል፡፡   በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለዓለም ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ናቸው ብለዋል፡፡ በተለይ ደግሞ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ የወሰደው እርምጃ ይበል የሚባል ነው ብለዋል፡፡ ሀገራቸው ይህንን ተግባር እንደምትደግፍም አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ሳምንት ከነገ ጥቅምት 4 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 6 ቀን 2018 በአዲስ አበባ ይካሔዳል፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ የብዙሃን ትራንፖርት፣ ባቡር፣ ኮሪደር ልማት፣ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች እንዲሁም በፖሊሲ ረገድ እያከናወነች ያለችውን ተጨባጭ ሥራ እንደምታቀርብም ተገልጿል።
ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ተረፈ ምርቶችን ወደ ሐብት በመቀየር ውጤታማ እየሆኑ ነው
Oct 13, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ተረፈ ምርቶችን ወደ ሐብት በመቀየር ገቢ ከማመንጨት ባለፈ በአካባቢ ጥበቃ እና በስራ ዕድል ፈጠራ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ገለጹ። በኢትዮጵያ በቅርቡ ብሔራዊ የሰርኩላር ኢኮኖሚ ፍኖተ ካርታ ይፋ የተደረገ ሲሆን ቆሻሻን መልሶ መጠቀምን ማስፋፋት፣ ለአካባቢ ተስማሚ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት እና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ላይ የተመሠረቱ የሥራ ዕድሎችን ማስፋት ከዋና ዓላማዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የአካበቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ እንደተናገሩት ለፍኖተ ካርታው ውጤታማነት የግል ዘርፉ ተሳትፎ የጎላ ነው።   ፍኖተ ካርታው ጽዱ ኢትዮጵያን ከማሳካት አንጻር የግሉ ዘርፍ ትልቁን ድርሻ እንዲወጣ የሚያስችል ነው ብለዋል። የግሉ ዘርፍ የሚያስፈልገውን የፋይናንስ፣ የቴክኖሎጂና ሌሎች ድጋፎች ያካተተ የተቀናጀ ስርዓት የሚዘረጋ መሆኑንም ተናግረዋል። ብሔራዊ የሰርኩላር ኢኮኖሚ ፍኖተ ካርታ ግቦችን ከማሳካት አንጻር ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ተረፈ ምርቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ለአካባቢ ተስማሚና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ምርቶችን በማምረት የጀመሩት ሥራ ምሳሌ ሆኖ የሚቀርብ ነው። ወጣት ሚካኤል ኃይሌ ጥቅም ላይ የዋሉ ወረቀቶችን በመሰብሰብና መልሶ በመጠቀም የተለያዩ ምርቶችን በማምረት ላይ እንደሚገኝ ይናገራል።   ምርቶቹም ለተቋማት ማስታወቂያ፣ ለጌጣጌጥ፣ ለስጦታና ለሌሎች አገልግሎቶች እየዋሉ መሆኑን ጠቁሞ የቆሻሻ አሰባሰብ ሂደቱን ከማህበረሰቡ ጋር በማስተሳሰር የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልጿል፡፡ ከየተቋማቱ የሚጣሉ ወረቀቶችን ለሚሰበስቡ ለበርካታ የጽዳት ሠራተኞችና ሴቶች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸውም አስረድቷል። ወጣት ኢያሱ መዝገቡ የሙዝ ልጣጭን ከሌሎች ግብዓቶች ጋር በመጠቀም ለቤትና ቢሮ ቁሳቁሶች፣ ለጫማ እንዲሁም ለተለያዩ የቆዳ ምርቶች የሚውል አካባቢን የማይጎዳ ቀለም እያመረተ መሆኑን ገልፅዋል።   የእንጨት ተረፈ ምርቶችን በመጠቀም በውስጡ የሚገኘውን መርዛማ ጋዝ በማውጣት ለጤና የማይጎዳ የከሰል ምርት እያመረተ እንደሚገኝ የተናገረው ደግሞ ወጣት ኢዮብ አለሙ ነው፡፡ ምርቱ ከእንጨት ተረፈ ምርት የሚመረት በመሆኑ የደን ጭፍጨፋን በመከላከል ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጿል።   ይህም የሀገሪቱን የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር እና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሥራዎችን በመደገፍ ረገድ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት አመልክቷል። ወጣቶቹ እንዳሉትም በቀጣይም ምርቶቻቸውን በስፋት በማምረት የሥራ ዕድል ፈጠራን ይበልጥ ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ገልጸዋል።    
በምዕራብ ወለጋ ዞን በክረምት ወራት ለተተከሉ ችግኞች የሚደረገው እንክብካቤ ቀጥሏል
Oct 11, 2025 178
ጊምቢ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን በክረምት ወራት ለተተከሉ ችግኞች የሚደረገው እንክብካቤ መቀጠሉን የዞኑ የግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። የምዕራብ ወለጋ ዞን የግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፈይሳ ሀምቢሳ እንደገለጹት በዞኑ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተተክለዋል።   ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች ውጤታማ እንዲሆኑ በዞኑ ነዋሪዎች የችግኝ እንክብካቤ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ወቅትም በተለይም ባለፈው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በተጠናከረ መልኩ እየተካሄደ ነው ብለዋል። በአጠቃላይ በዞኑ ባለፉት ዓመታት በተከናወነ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች አካባቢውን አረንጓዴ ከማልበስ ባለፈ ለግብርና ስራም እገዛ እያደረጉ መሆኑ ገልጸዋል። በችግኝ እንክብካቤው እየተሳተፉ ከሚገኙ መካከል ወይዘሮ ለሊሴ ብርሃኑ፣ በክረምት ወራት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን እየተንከባከቡ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በአካባቢያቸው በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተተከሉ ችግኞች ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ መሆኑን በመገንዘባቸው አሁንም በእንክብካቤው መጠንከራቸውን ጠቅሰዋል። አቶ ገረመው ነገራ በበኩላቸው የተተከሉ ችግኞች ለውጤት እንዲበቁ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል።   ሁሉም በየአካባቢው ችግኞችን በመንከባከብ ለውጤት ማብቃት አለበት ያሉት ደግሞ አቶ ነጻነት አበበ ሲሆኑ ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች የተለያየ ጥቅም እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል።  
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያሏትን ተሞክሮዎች የምታቀርብበት አህጉራዊ ሁነት
Oct 10, 2025 259
አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ “ አፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ዊክ 2025” የተሰኘ የአፍሪካ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ሳምንት ከጥቅምት 4 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል። ሳምንቱ “ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የትራንስፖርት ስርዓትን ማረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ይካሄዳል። ተቀማጭነቱን ኬንያ ናይሮቢ ያደረገው ”አፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ አሊያንስ” የተሰኘ ድርጅት፣ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር፣ የተባበሩት መንግስታት የአካባቢ ጥበቃ ፕሮግራም እና ሌሎች አጋሮች ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተዋል።   በሁነቱ ላይ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ኢኖቬተሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የትራንስፖርት ዘርፍ መሪ ተዋናያን ይሳተፋበታል። ሳምንቱ አፍሪካ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽርካሪዎች የምታደርገውን ሽግግር ማፋጠን ዋንኛ ትኩረቱ አድርጓል። የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን በአረንጓዴ ትራንስፖርት ሳምንቱ ላይ ከ500 በላይ ሰዎች በአካል እና ከ2000 በላይ ሰዎች በበይነ መረብ አማራጭ እንደሚሳተፉ ለኢዜአ ገልጸዋል። በሳምንቱ ላይ ከ30 በላይ የውይይት መድረኮች እና አውደ ርዕዮች እንደሚካሄዱ ጠቅሰው ከነዚህም አንዱ የአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት የሚገኙበት መድረክ እንደሆነ ተናግረዋል። አረንጓዴ ትራንስፖርትን የተመለከቱ የጥናት ውጤቶች እና ግኝቶች ይፋ እንደሚደረጉም ነው የገለጹት። ከሁነቶቹ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪ ጉብኝት መርሃ ግብር እንደሚኖር ጠቅሰው ከ200 በላይ ተሳታፊዎች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ገጣጣሚዎችን፣ የኤሌክትሪክ ባሶች እንቅስቃሴ፣ የተሰሩ የኃይል መሙያ ማዕከላት፣ ዴፖዎች እንዲሁም በሽያጭ፣ አቅርቦት እና ጥገና የተሰማሩ አካላትን እንቅስቃሴ እንደሚጎበኙ አመልክተዋል። በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተካሄደው “ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2024” ዓለም አቀፍ አውደ ርዕይና ሲምፖዚየም ላይ የተነሱ አጀንዳዎች አፈጻጸም እንደሚገመገምም እንዲሁ። የትራንስፖርት ሳምንቱ አካል የሆነ የ1 ሺህ 600 ኪሎ ሜትር የኤሌክትሪክ መኪና ጉዞ በመካሄድ ላይ መሆኑን ጠቅሰው ተጓዦቹ ዛሬ ሶስተኛ ቀናቸውን እንደያዙና የፊታችን እሁድ አዳማ እንደሚደርሱ ጠቁመዋል። ጉዞው በኤሌክትሪክ መኪናዎች አማካኝነት ቀጣናዊ የትራንስፖርት ስርዓትን መፍጠርን ያለመ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ በማድረግ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን የማስፋት ስራ እያከናወነች እንደምትገኝም ነው ሚኒስትር ዴኤታው የገለጹት። በኢትዮጵያ መንገዶች ላይ ካሉ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ተሽከርካሪዎች መካከል ከ115 ሺህ በላይ የኤሌክትሪክ መኪኖች እንደሚገኙበት ጠቁመው ይህም ከአጠቃላይ ተሽከርካሪዎች የሰባት መቶ ድርሻ እንደያዙ ጠቁመዋል። የግሉን ዘርፍ እና የተለያዩ አካላትን በማሳተፍ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የተሽከርካሪዎች ኃይል መሙያ ጣቢያዎች መገንባታቸውን ነው ያብራሩት። በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት 16 ተቋማት የኤሌክትሪክ መኪናዎችን እየገጣጠሙ መሆናቸውን ጠቅሰው የአረንጓዴ ትራንስፖርት በህዝብ ትራንስፖርት ላይ እየሰፋ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ አውቶቢሶች የማስፋት ስራ ውጤት እያስገኘ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው መንግስት በኤሌክትሪክ መኪና ለተሰማሩ አካላት የታክስ ማበረታቻ ማድረጉንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት በፖሊሲ እና ስትራቴጂ በመደገፍ ውጤታማ ስራን እያከናወነች እንደምትገኝና ይህንንም መልካም ተሞክሮዋን በአህጉራዊው ሁነት ላይ እንደምታቀርብ አመልክተዋል። የትራንስፖርት ሳምንቱ አካል የሆነ የወጣቶች ጉባኤ በበይነ መረብ መካሄዱንና በዚህም መደረክ ላይ ኢትዮጵያ ያላትን ተሞክሮ ለአፍሪካ ሀገራት ማቅረቧን ገልጸዋል። የአፍሪካ አረንጓዴ ትራንስፖርት ሳምንት አህጉሪቷ ከብክለት የጸዳ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓት ለመፍጠር ለምታደርገው ጥረት አቅም የሚፈጥር መሆኑ ተመላክቷል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በሙሉ አቅም መተግበር ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው - መሐመድ አሊ ዩሱፍ
Oct 10, 2025 250
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ሙሉ ለሙሉ ገቢራዊ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 24ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሁነቶች በአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት እና ተወዳዳሪነት ተጽእኖ እያሳደሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከመቼው ጊዜ በላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሙሉ ለሙሉ በአፋጣኝ መተግበር እንደሚገባው የሚያመላክት ነው ብለዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ከቀረጥ ጋር ያልተያያዙ የንግድ ገደቦችን በማንሳት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተሳለጠ የንግድ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችሉ ማዕቀፎችን በመተግበር ለአጀንዳ 2063 መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኮሜሳ፣ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (ሳዴቅ) እና የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ (ኢኤሲ) የሶስትዮሽ ትብብር ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ማዕቀፉ የትስስር አጀንዳ ተምሳሌት እና አንድ የሆነች፣ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች አህጉር ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ የተስፋ ብርሃን ፈንጣቂ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር ቀጣናዊና አህጉራዊ የትስስር አጀንዳዎችን ትግበራ ለማፋጠን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንደሚያጠናክሩ ገለጹ
Oct 10, 2025 247
አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን የቆየ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። ጀርመን ለኢጋድ ቀጣና የተለያዩ የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፎችንም ይፋ አድርጋለች። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በልማት ትብብራቸው ዙሪያ በጅቡቲ ስትራቴጂካዊ ምክክር አድርገዋል።   በምክክሩ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር እና ልማት ሚኒስቴር የምስራቅ አፍሪካ ዘርፍ ኃላፊ ሃኒንግ እና በጅቡቲ የጀርመን አምባሳደር ሄይከ ፉለር (ዶ/ር) ተገኝተዋል። ስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ የግንኙነት ማዕቀፎች ላይም መክረዋል። ፍልሰት እና አየር ንብረት ለውጥ የውይይቱ አበይት ማጠንጠኛዎች ናቸው። ሁለቱ ወገኖች የጀርመን ቀጣናዊ የፍልሰት ፈንድ ዳግም ማዋቀር ሂደት መልካም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በማንሳት የኢጋድ የቀጣናዊ የፍልሰት ፖሊሲ ማዕቀፍ ፣ የነጻ እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፎች እና የዜጎችን የአኗኗር ሁኔታ የማጠናከር ስራ ለመደገፍ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ጀርመን ለኢጋድ የፍልሰት ፖሊሲ ትግበራ ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ ትግበራ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ ቃል መግባቷን ኢዜአ ከቀጣናዊ ተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም ጀርመን በኢጋድ አባል ሀገራት ለሚከናወኑ የማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ስራዎች በቀጣናዊ የአደጋ ፋይናንስ ፕሮግራም አማካኝነት 22 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ መዘጋጀቷ ተመላክቷል። የፋይናንስ ማዕቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ድንገተኛ አደጋዎችን የመከላከል ስራዎች የሚደገፍ እና የኢጋድ የድርቅ አደጋን የመቋቋም እና ዘላቂነት ኢኒሼቲቭ ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን የሚደግፍ ነው። በስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች ውጤት ተኮር፣ አሳታፊ እና ተጠያቂነትን መሰረት ያደረገ አጋርነትን መፍጠር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢጋድ እና ጀርመን ትብብራቸውን ለማጠናከር፣ የጋራ ስራዎቻቸው የአባል ሀገራት የቅድሚያ ትኩረቶች ያማከሉ እንዲሆኑና የፖሊሲ ምክክራቸውን በመደበኛነት ለማከናወን ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ኢጋድ እና ጀርመን 37 ዓመታትን ያስቆጠረ አጋርነት እንዳላቸው መረጃዎች ያመለክታሉ።
የአፍሪካ ህብረት የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 7, 2025 312
አዲስ አበባ፤ መስከረም 27/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷ ወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን አስታወቀ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት ከፍተኛ አመራሮች ከሆኑት ዲያላ ሞሙኒ እና አህመድ ቤኒንግ ጋር በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።   የአፍሪካ ህብረት የወጣቶች ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ሊቀ መንበር ኡቺዚ ምካንዳዋየር በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል። የአፍሪካ ህብረት ስምምነቱ የአህጉሪቷ ወጣቶች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና ወጣቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። በስምምነቱ አማካኝነት የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት በሀገራት ደረጃ ያሉ የወጣት ምክር ቤቶች የሚያቀናጅ አህጉራዊ ማዕቀፍ እና ለአፍሪካ ወጣቶች እንደ ጋራ ድምጽ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ንቅናቄ የወለደው አህጉራዊ አደረጃጀት ሲሆን እ.አ.አ በ1962 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በጊኒ ኮናክሪ ባደረጉት ስብስባ ህብረቱን አቋቁመዋል።   ህብረቱ የተመሰረተው በወቅቱ ወጣቶች አፍሪካ ከቅኝ ግዛት እንድትላቀቅ ለነበረው ትግል አቅም እንዲሆኑ ከማሰብ የመነጨ ነው። የወጣቶች ህብረቱ እንቅስቃሴ የፖለቲካ ድጋፍን በማሰባሰብ እና የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዲወጡ በማድረግ ረገድ ስትራጂካዊ ሚናውን ተጫውቷል። የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት እ.አ.አ በ2006 ባደረገው ስብስባ የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በድጋሚ የማደራጀት የውሳኔ ሀሳብ በማፅደቅ ህብረቱ የአህጉሪቷ የወጣት መዋቅር እንዲሆን በይኗል።
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አፍሪካ በዓለም መድረክ ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት ድጋፉን ሊሰጥ ይገባል- አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Sep 24, 2025 888
አዲስ አበባ፤ መስከረም 14/2018(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አፍሪካ በዓለም መድረክ ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት እያደረገችው ላለው ጥረት ድጋፍ እንዲሰጥ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጥሪ አቀረቡ። 80ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ከጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም አንስቶ በድርጅቱ ዋና መቀመጫ ኒውዮርክ እየተካሄደ ይገኛል። የጠቅላላ ጉባኤው አካል የሆነ ከፍተኛ የምክክር እና ክርክር መድረክ ዛሬ በኒው ዮርክ ተጀምሯል። “'ደህናነት በአብሮነት፤ 80 ዓመታት እና ከዚያ በላይ ለሰላም፣ ለልማት እና ለሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ” በሚል መሪ ሀሳብ ነው ጉባኤው የሚካሄደው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ “እየተለወጠ ባለው የዓለም የፖለቲካ ስርዓት ውስጥ የአፍሪካ ምልከታዎች” በሚል መሪ ሀሳብ ለጉባኤው ተሳታፊዎች የቪዲዮ መልዕክት አስተላልፈዋል። አምባሳደር ሳልማ በመልዕክታቸው አፍሪካ በተለያዩ መስኮች ራሷን ለመቻል እያከናወነቻቸው ያሉ ስራዎች ፍሬ እያፈሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች በራሷ ፋይናንስ በማድረግ ረገድ ለውጥ ማምጣቷን በማሳያነት ጠቅሰው የአፍሪካ የሰላም እና ደህንነት ማዕቀፍ በአፍሪካውያን ገንዘብ እና ባለቤትነት እየተመራ እንደሚገኝም አመልክተዋል። የአፍሪካ ህብረት የሰላም ፈንድ በአፍሪካውያን በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በትግበራ ላይ መሆኑን አንስተዋል። አምባሳደሯ በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ላይ ያላቸውን ሀሳብ ያጋሩ ሲሆን የንግድ ቀጣናው ዜጎች እና ገበያን ከማስተሳሰር ባለፈ ሰው ሰራሽ ድንበሮች በእኛ ላይ ከመጫናቸው በፊት የነበረውን የንግድ ትስስር እና ትብብር እንደሚመለስ ተናግረዋል። አፍሪካ በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረክ ያላት ድርሻ እያደገ መምጣቱን ገልጸው አህጉሪቷ በቡድን 20 ቋሚ መቀመጫ ማግኘቷ አበይት ማሳያ ነው ብለዋል። አፍሪካ በቡድን 20 ውስጥ ያገኘችው ቋሚ መቀመጫ ለዓለም ችግሮች መፍትሄ ያላትን አይተኬ ሚና በግልጽ የሚያመላክት እንደሆነም ተናግረዋል። እየተለወጠ ያለው የዓለም ስርዓት ለአፍሪካ በርካታ እድሎችን ይዞ መጥቷል ያሉት ምክትል ሊቀመንበሯ ይህን መልካም አጋጣሚ ለመጠቀም እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። አምባሳደር ማሊካ ዓለም አቀፍ አጋሮች አፍሪካ የዓለም የፋይናንስ ስርዓት እኩልነት የሰፈነበት እንዲሆን እና በተባበሩት መንግስታት የጸጥታ ምክር ቤት ውክልና እንድታገኝ እያነሳች ያለው ፍትሃዊ ጥያቄ እና እውነተኛ መሻት እንዲደግፍ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። አፍሪካ ከዓለም ጋር ያላት ትብብር በጋራ መከባበር እና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸው አፍሪካ ስታድግ የዓለም ብልጽግና እና መረጋጋት ይረጋገጣል ሲሉም ተናግረዋል።
ሐተታዎች
 ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 273
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም።   በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል።   የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል።   በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል።   ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል።   በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።   በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 490
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።  
  "ያሆዴ"- ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት
Sep 28, 2025 583
(በማሙሽ ጋረደው - ከኢዜአ ሆሳዕና ቅርንጫፍ) የሀዲያ የአዲስ ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው። ለማህበራዊ የህይወት አመራር ጉልህ አስተዋጾም ስላለውም በሀዲያዎች ዘንድ በየዓመቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል፡፡ "ያሆዴ" ያለፈውን አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲስ ዘመን የሚቀበሉበት፤ የመጻኢ ተስፋ ብስራትና የልምላሜ ምልክትም ጭምር ተደርጎም ይቆጠራል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሲቀርብ የሀዲያ ተወላጆችና የበዓሉ ተሳታፊዎች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከያሉበት ወደአካባቢው በመምጣት ይሰባሰባሉ፡፡ በዘንድሮ የያሆዴ በዓልም የሀድያ ተወላጆች የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ በተዘጋጀ ስፍራ (ነፈራ) ተሰባስበው በዓሉን በድምቀት አክብረውታል፡፡ በበዓሉ አከባበር ያለፈው ዓመት ስኬትም ይገመገማል፤ በአዲሱ ዓመትም የተሻለ ተሰርቶ ስኬት እንዲመዘገብ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት ይካሄዳል። ሊተገበር የሚችል ዕቅድም ይታቀዳል፡፡ በግልና በቤተሰብ የመጡ ስኬቶች በጋራ በመሆን ይገመገማሉ። የበረቱና ውጤት ያስመዘገቡም እንዲበረታቱ ይደረጋል። ለዚህም ነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው የሚባለው። ሰዎች እንዲሰሩና ስኬት እንዲያስመዘግቡ የሚያበረታታ እሴት አለው። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፋን ቦጋለ እንደሚሉት የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል "ያሆዴ" ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት ነው፡፡ ከነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የበዓሉ መቃረብን የሚያበስሩት ታዳጊ ልጆች ናቸው። ልጆቹ የዋሽንት (ገምባቡያ) ድምጽ ማሰማት ከጀመሩ በጉጉት የሚጠበቀውን የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል መድረሱ ምልክት ነው። በዓሉ ሀድያዎች አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበት ወቅት ነው። በዓሉ የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት በመሆኑም የተለየ ትርጉምና ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች ተራርቀው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት ከያሉበት ይሰባሰባሉ። በዓሉ በአማረ መልኩ እንዲከበርም ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻቸውን ያከናውናሉ።   አባውራዎች ለበዓሉ ሠንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በቱታ ወይም በቅርጫ ቡድናቸው አማካኝነት እየቆጠቡ ይቆያሉ። እንዲሁም ለእንስሳት የሚሆን የግጦሽ ሳር የሚያበቅል ቦታ ከልለው ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሚሆነበት ምክንያት ደግሞ በዓሉ በሚከበርበት ሰሞን የሰው ልጅ ይቅርና እንስሳትም መጥገብ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ እማውራዎች ከበዓሉ ሦስትና አራት ወራት አስቀድመው እንሰት በመፋቅ ቆጮና ቡላ ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም ከአካባቢው እናቶች በጋራ በመሆን (ዊጆ) የተሰኘ የቅቤ እቁብ በመግባት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ማጠራቀም ይጀምራሉ፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ ለአተካናና ለሥጋ መብያ ናቀሮ ወይም ዳጣን እንዲሁም የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት ድርሻ የእናቶች ነው፡፡ ለበዓሉ የቤት ውስጥና የውጭ ግርግዳን በቀለምና በተለያዩ ጌጣጌጦች የማስዋብ ሃላፊነት ደግሞ የልጃገረዶች ነው። ወጣት ወንዶች ከነሀሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚያሳዩዋቸውን ግንድ በመቁረጥ ለምግብ ማብስያ እንዲውል ፈልጠው ያዘጋጃሉ። በሀዲያዎች አጠራር ለችቦ የሚሆን እንጨት ወይም ጦምቦራ ከጫካ ለቅመው አስረው እንዲደርቅም ያስቀምጣሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት የሚያደርገው ጥረት በዓሉ በስኬትና በድምቀት እንዲከበር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በዚህም ያሆዴ ከተናጠል ይልቅ ትብብርን የሚያጠናክር ነው ማለት ይቻላል። እሴቱ በትብብር መድመቅ እንደሚቻልም የሚያሳይ ነው።   ይህን ሀሳብ የሚጋሩት አቶ መስፍን የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል በምንም ሁኔታ መነጣጠል የማይቻል ትስስርን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ። ሀገራዊ አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር ዘመናትን የተሻገረና ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ባህላዊ እሴት ያለው መሆኑንም ይናገራሉ። በዓሉ ሊከበር ጥቂት ቀናት ሲቀረው አባውራዎች በቅርጫ ማህበራቸው አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ የእርድ በሬ ይገዛሉ። በዚህ ወቅት ገንዘብ ማዋጣት ያልቻሉ የቅርጫ አባላት እህል በሚደርስበት ወቅት ለመክፈል ተስማምተው በሬውን በዱቤ እንዲገዙ ይደረጋል፡፡ ይሄም የሚሆነው በያሆዴ በዓል አንዱ ሲበላ ሌላው ተመልካች መሆን ስለሌለበት ነው። እርስ በርስ መጨካከን እንዳይኖርና በዓሉን በአብሮነት ሁሉም ተደስቶ ማክበር እንዲችል ለማድረግ ነው። ከበዓሉ ዕለት በፊት ያለው የመጨረሻ ገበያም የእብድ ገበያ (መቻዕል ሜራ) የሚል ስያሜ አለው። ይሄ ሥያሜ ያገኘው በዓሉ ሲቃረብ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ውጥረት ታሳቢ በማድርግ ነው፡፡ በዚህ የእብድ ገበያ ህብረተሰቡ መገበያየት የሚጀምረው ጠዋት ማለዳ ጀምር ሲሆን የግብይት ሂደቱ የሚጠናቀቀው ደግሞ እኩለ ቀን ላይ ነው፡፡ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለመግዛትና የያሆዴ በዓል ከተከበረ በኋላ ለአንድ ወር ገበያ ስለማይቆም ይህን ታሳቢ ያደረገ ግብይት ለመፈጸም የግብይት ሂደቱ ጥድፊያ የበዛበት ሆኖ ይታያል።   ያሆዴ በዓል መከበር የሚጀምረው በአተካን ሂሞ ወይም በአተካና ምሽት ሲሆን ይህም ከበዓሉ አንድ ቀን በፊት ያለው ምሽት ነው። ስያሜውን ያገኘው "አተካና" ከተሰኘና በያሆዴዎች ዘንድ ለክብር እንግዳ እና በዘመን መለወጫ ከሚዘጋጅ ምግብ ነው። አተካና ከወተት፣ ከአይብ፣ ከቡላ፣ ከቅቤና ከሌሎች የቅመማ ቅመም ውጤቶች የሚዘጋጅ ምግብ ሲሆን በጣም ጣፋጭና የምግበ ፍላጎትን የሚጨምር ምግብ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ይሄንን የተለየ ምግብ ተሰባስቦ በአብሮነት በመመገብ በደመቀ መልኩ በዓሉን ማክበር ይጀምራል፡፡ የአካባቢው አባቶች በወጣቶች የተዘጋጀ የማቀጣጠያ እንጨት (ሳቴ) ይዘው ትልቅ በሚባሉ አባውራ ቤት ደጃፍ ወደ ተዘጋጀው የችቦ ደመራ (ጦምቦራ) ቦታ ይመጣሉ:: የሀገር ሽማግሌች አዲሱ ዓመት የብርሃን ዓመት እንዲሆን፤ ለሀገርና ለህዝቦቿ ሰላም እንዲጸና፤ አብሮነት እንዲጠናከር፣ ሰላምና ፍቅር እንዲነግስ ፈጣሪያቸውን ከተማጸኑ በኋላ ችቦውን በእሳት ይለኩሳሉ፡፡   ችቦው ከተለኮሰ በኋላ የአካባቢው ወጣቶች ተሰባስበው ያሆዴ …ያሆዴ! …ያሆዴ! በማለት እየጨፈሩ ያነጋሉ ይጨፍራሉ:: በሀድያዎች ዘንድ "ያሆ" ማለት የአዲስ ዓመት መግባትን ተከትሎ ማብሰሪያ ጭፈራ ሲሆን "ኤዴ" ማለት ደግሞ አገናኝ ማለት ነው፡፡ በያሆዴ በዓል የእርድ ሥነ ስርዓት ለማከናወን ነዋሪዎች የሚሰበሰቡበት ስፍራ "ነፈራ" የሚል ስያሜ አለው። የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሰፋ ያለ ቦታ ሰሆን በተለያዩ የጥላ ዛፎች የተዋበና ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀም ነው። በእለቱ ለእርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኋላ የባህል ሽማግሌዎች የበሬውን ሻኛ በሰርዶ ሳር ለጋ ቅቤ ይቀባሉ፤ ወተትም ያፋሱበታል፡፡ ይህ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ጋቢማ የሚባል ሲሆን (የመልካም ምኞት) መግለጫ ስነ ስርዓትም ነው፡፡ ይህም ሥነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም "ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሀገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን " እያሉ በአባቶች ምርቃት ከተካሄደ በኋላ የእርድ ስነ ስርዓት ይከናወናል፡፡ የእርድ ሥነ ስርዓቱ የተከናወነበት ቤት እማወራ አስቀድመው ባደረጉት ዝግጅት መሰረት ቅቤ፤ (ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ) እንዲሁም ከታረደው የበሬ ሥጋ አርዚ ማራ (ቅምሻ) ይወሰድና ክትፎ ከተዘጋጀ በኋላ በጋራ እየበሉ እየተጫወቱ ይውላሉ፡፡ በዚህም በቅርጫ ሥጋው ላይ ከሚሳተፉት የቤተሰብ አባላት ውጪ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችም ጭምር አብረው በመብላት በመጠጣት በዓሉን በአንድነት ያሳልፋሉ፡፡ ቀሪውን የቅርጫ ሥጋም አባላቱ ተከፋፍለው ወደ እየቤታቸው ይወስዱታል፡፡ በዓሉ አብሮ የመብላት፣ የመጠጣት፣ የመጠያየቅ፣ ችግርንና ግጭትን በጋራ ተወያይቶ የመፍታት፣ መፈቃቀርና መተሳሰብን የሚፈጥር፣ አቅመ ደካሞችና የተቸገሩ የሚረዱበት የአብሮነት መገለጫ በመሆኑ በተለየ መልኩ ይከበራል፡ ከእርድ ሥርዓቱ በኋላ በማግስቱ ልጆች አደይ አበባ (ዘራሮ) ይዘው ወደ ወላጆቻቸው እየጨፈሩ ይመጣሉ። የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባላሉ። ከስጋውም፣ ከቦርዴውም፣ ከአተካናውም እንዲመገቡ ያደረጋል። ይህ ስነ ስርዓትም ሚክራ ይባላል። በያሆዴ የዘመን መለወጫ በዓል ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ሥጋና አደይ አበባ ጭምር ይዘው ይሄዳሉ። በዓሉ ያላገቡ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ለአዲስ ህይወት ጅማሬ የሚያበስሩበት በመሆኑን የተለየ ድባብ አለው፡፡ የያሆዴ በዓል ካሉት እሴቶች አንዱ የህብረተሰቡን የአካባቢ ልማት ተሳትፎ ማበረታታት ተጠቃሽ መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ዕሴቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናቅቀው ለማህበረሰብ ጥቅም እንዲውሉ ጭምር አቅም እየሆነ መምጣቱን ነው የሚናገሩት።ይህ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የማህበራዊ መስተጋብር መጋመጃ የሆነው በዓል እሴቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል መስራት ይገባል። እሳቸው እንዳሉት በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማስቻል እየተሰራ ነው፡፡ ለዚህም መምሪያው ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ዕሴቱን የመሰነድና ምርምሮች ማካሄድን ጨምሮ እያከናወናቸው ያሉ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።  
80ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ እና የኢትዮጵያ ተሳትፎ
Sep 27, 2025 703
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ግዙፉና ጉምቱው የዓለም የብዝሃወገን ዲፕሎማሲ መድረክ ነው። 80ኛው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ከጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም አንስቶ “ደህናነት በአብሮነት፤ 80 ዓመታት እና ከዚያ በላይ ለሰላም፣ ለልማት እና ለሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። የጠቅላላ ጉባኤው አካል የሆነ ከፍተኛ የምክክር እና ክርክር መድረክ ከመስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተደረገ ነው። ከሰላም እስከ አየር ንብረት ለውጥ፣ ከዘላቂ ልማት እስከ ዲጂታል አካታችነት፣ ከሰብዓዊነት እስከ የዓለም የኢኮኖሚ አወቃቀር፣ በዓለም መድረክ ፍትሐዊ ውክልናን ከማግኘት እስከ ዓለም በቀጣይ ምን ትሆን? ድረስ በርካታ ጉዳዮች ተነስተው ውይይቶችና ክርክሮች በማድረግ ለወደፊቱ ይበጃሉ የተባሉ ሀሳቦች በመነሳት ላይ ይገኛሉ። በጉባኤው ይፋዊ መክፈቻ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ባደረጉት ንግግር ዓለም በተለያዩ ሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች፣ ድህነት፣ ረሃብ፣ ጦርነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣የኢኮኖሚ ቀውስ እየተፈተነች ባለበት ወቅት የሚከበረው የተመድ 80ኛ ዓመት አባል ሀገራት ከመቼውም ጊዜ በላይ አብሮነታቸውን በማጠናከር የተሻለች ዓለም ለመፍጠር በጋራ መሥራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል። የተመድ ሥርዓትንና መዋቅር 21ኛው ክፍለ ዘመን በሚመጥን ልክ መለወጥ እንደሚገባ አመልክተዋል። ዋና ፀሐፊው ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምርጫውን ሰላም፣ ፍትህ ዘላቂ ልማት እና ሰብአዊ ክብር ሊያደርግ እንደሚገባና ለተግባራዊነቱም ቁርጠኝነት እንዲያሳይ ጥሪ አቅርበዋል። በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በጠቅላላ ጉባዔው ላይ ተሳትፎ እያደረገ ነው።   ልዑካን ቡድኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራን ጨምሮ ከፍተኛ ባለስልጣናትን አካቷል። ኢትዮጵያ በጉባዔው ላይ የራሷን ብሔራዊ ጥቅሞች እና የአፍሪካን ጥቅሞች በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ንቁና ጠንካራ ተሳትፎ እንደምታደርግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ከዋናው ጉባዔ ተሳትፎ በተጨማሪ በርካታ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን የጎንዮሽ የውይይት መድረኮች ላይም ኢትዮጵያ የራሷን ብሄራዊ ጥቅሞች ቅድሚያ እየሰጠች እንደምትሳተፍም አመልክዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከጉባኤው ጎን ለጎን ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ጋር ተወያይተዋል። ዋና ፀሐፊው ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠናቃ በመመረቋ ፣ የአየር ንብረት ጉባዔ እና ሌሎች ፕሮጀክቶችን በማስተናገድ ላስመዘገበችው ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። ሁለቱ ወገኖች በቀጣናው እና በሌሎች ጉዳዮች ላይም ተወያይተዋል። በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ ከተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ፕሬዝዳንት አናሌና ባርቦክ ጋር ተወያይተዋል።   ሁለቱ መሪዎች በወቅታዊ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች እና በባለብዙ ወገን ግንኙነት ላይ እያሳደረ ስለሚገኘው ተጽዕኖ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ የባለብዙ ወገን ግንኙነት እና የጋራ ደኀንነት መርሆዎችን ለማስጠበቅ የጋራ ጥረቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በቅርቡ የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የተመድ ዘላቂ ልማት ግቦችን ከማሳካት ረገድ በተለይም ግብ ሰባትን ለማሳካት ግድቡ ንጹሃ የኃይል አቅርቦት ከማሳደግ አኳያ ያለውን ፋይዳ ገልጸዋል። ፕሬዝዳንት አናሌና ባርቦክ በበኩላቸው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተር መርሆዎችን ማክበር እና መጠበቅ ለዓለም ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያ ልማት፣ ቀጣናዊ ሰላም እና ደኀንነትን ጨምሮ በተለያዩ ቀጣናዊ የትኩረት መስኮች ላይም መክረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ ከጉባኤው ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ጋር የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ ይገኛል።   አምባሳደር ሃደራ ከደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መንደይ ሲማያ ኩምባ የኢትዮጵያ እና ሱዳን የሁለትዮሽ ኢኮኖሚያዊ ግፍንኙነት ማጠናከር እንዲሁም በቀጣናዊ እና በባለብዙ ወገን የትብብር መድረኮች የተባበረ አቋም እንዲኖራቸው ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መክረዋል። ከሞዛምቢክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሪያ ማኑኤላ ዶስ ሳንቶስ ሉቃስ ጋርም ተወያይተዋል። ሽብርተኝነትን መከላለከል፣ አቪዬሽን እና ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። አምባሳደሩ ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ ባለሥልጣን አምባሳደር ጆናታን ፕራት ጋር በሀገራቱ የጋራ ፍላጎቶች ላይ ተወያይተዋል። ሁለቱ ወገኖች በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የንግድ ግንኙነት ማሻሻል የሚያስችሉ ሥራዎችን ለማከናወን ተስማምተዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ከአውሮፓ ከአውሮፓ ሕብረት የውስጥ ጉዳይ እና የፍልሰት ኮሚሽነር ማግነስ ብሩነር ጋርም የተወያዩ ሲሆን ሁለቱ ወገኖች ዓለም አቀፍ ፈተና በሆኑ ከፍልሰት ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። አምባሳደሩ ከተባበሩት አረብ ኢምሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሼክ ሻክቦት ቢን ናህያን አል ናህያን ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የበለጠ በሚያጠናክሩ ዕድሎች እንዲሁም በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር የበለጠ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። አምባሳደር ሃደራ አበራ ከኩባ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሩኖ ሮድሪጌዝ ፓሪላ ጋር በሁለትዮሽ ትብብር ዙሪያ መክረዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ከአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጄሁን ቤራሞቭ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው አገራት መሆናቸውን በመጥቀስ ሁለቱ አገራት በተለይ በኢኮኖሚ ዘርፎች ይበልጥ ተቀናጅተው ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ገልፀዋል። ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው ሀገራቱ በንግድ፣ በኢንቬስትመንት፣ በቱሪዝም በግብርናና በትምህርት ዘርፎች እንዲሁም በባለብዙ ወገን መድረክ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል። ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ጉባኤው ጎን ለጎን ባሉ የጎንዮሽ ውይይቶች ላይ እየሳተፈች ይገኛል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተሳተፉበት መድረክ ኢትዮጵያ የአፍሪካን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ማስፋት አላማ ያደረገው “Mission 300” ኢኒሼቲቭ ተቀላቅላለች። በዓለም ባንክ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ የሚመራው ኢኒሼቲቭ እ.አ.አ በ2030 በአፍሪካ የሚገኙ 300 ሚሊዮን ዜጎችን በኤሌክትሪክ ኃይል የማስተሳሰር ውጥን ያለው ነው። ፕሮጀክቱ የአፍሪካ መንግስታት፣ የግሉ ዘርፍ እና የልማት አጋሮችን ያሳተፈ ሲሆን በአፍሪካ አስተማማኝነቱ የተረጋገጠ፣ አካታች እና ተመጣጣኝ የኢነርጂ አቅርቦትን ተደራሽ በማድረግ የኢኮኖሚ እድገት እና ቀጣናዊ ትስስርን የማጠናከር አላማንም አንግቧል። ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ያላትን እምቅ አቅም ለመጠቀም እና ቀጣናዊ የኃይል ትስስሯን ለማሳደግ ወሳኝ ሚና እንዳለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ የንጹህ ኢነርጂ ሽግግር ውስጥ ያላትን የመሪነት ሚና እንደሚያሳድግና አፍሪካ ከኢነርጂ ድህነት የማላቀቅ እና ዘላቂ ልማትን የማረጋገጥ ትልም ለማሳካት እንደሚያግዝም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በአፍሪካ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (ሲዲሲ አፍሪካ) ኮሚቴ አባል የመሪዎች ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል። ሚኒስትር ዴኤታው በስብሰባው ላይ ኢትዮጵያ የጤናን ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥ የሀብት ማሰባሰብ እና ፈጠራ የተሞላበት የፋይናንስ ግኝት እንደምትከተል አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በጠቅላላ ጉባኤው ብሔራዊ ጥቅሞች እና የአፍሪካን ጥቅሞች በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ንቁና ጠንካራ ተሳትፎ ማድረጓን እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ገልጸዋል። በጉባኤው ላይ የኢትዮጵያን ልዑክ የመሩት ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የጉባኤው አካል በሆነው ከፍተኛ የምክክር እና ክርክር መድረክ ላይ ንግግር አድርገዋል። ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው በመልክዓ ምድራዊ ሁኔታዎች ምክንያት የትኛውም ሀገር የእድገት፣ የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ዕድሎች ዝግ መሆን የለበትም ሲሉ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር በመሆን በቀይ ባሕር እና በሕንድ ውቅያኖስ አካባቢ የሚገኙ ሁሉም ሀገሮች እኩል ልማት እና ደኀንነትን ማረጋገጥ ወደሚያስችል ሁለንተናዊ አሠራር እንዲዘረጋ ትሠራለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ይህንን ሕጋዊ ፖሊሲዋን ለማሳካትም የዲፕሎማሲያዊ እና ሰላማዊ አማራጮችን እንደምትከተል አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ፕሬዝዳንቱ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤትን ለማሻሻል አስቸኳይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። በማሻሻያውም ለአፍሪካ ውክልና በምክር ቤቱ በሁለቱም በኩል ቅድሚያ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበው፤ ለአፍሪካ የረጅም ጊዜ የፍትሕ መሻት ጥያቄ አቋራጭ ወይም ግማሽ መፍትሔ እንደሌለ አስገንዝበዋል። ከታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘም፤ የናይል ወንዝ የትብብር ማዕቀፍ በፈረንጆቹ ጥቅምት 2024 ወደ ተግባር መግባቱን እና የናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን ወደ መቋቋም ደረጃ መቃረቡን አስረድተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ መመረቁ፤ በኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ላልሆኑ ኢትዮጵያውያን ንጹህ የኃይል ምንጭ እንዲያገኙ የሚያደርግ መሆኑን አስገንዝበዋል። ግድቡ በከባድ የውኃ እጥረት ውስጥ ለሚኖሩ ወገኖቻችን ንጹህ ውኃ ለማቅረብ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና አጠቃላይ ልማትን እውን ለማድረግ አቅማችንን ያሳድጋል ብለዋል ፕሬዚዳንቱ። ግድቡ ለሰፋፊ ክልላዊ ትስስር ተስፋን የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ 1945 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሲመሰረት መስራች አባል ከነበሩት ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ይህም ኢትዮጵያ የባለብዝሃ ወገን እና ዓለም አቀፍ ትብብር ያላትን የማይናወጥ አቋም እና የጸና ቁርጠኝነት በግልጽ የሚያሳይ ነው። ኢትዮጵያ በዘንድሮው ጉባኤ ሰላም፣ ደህንነት፣ ዘላቂ ልማት እና የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ በዓለም አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ያራሷ እና የአፍሪካን ድምጽ በማሰማት የነቃ ተሳትፎ እያደረገች ትገኛለች። 80ኛው የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም ይጠናቀቃል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 793
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1616
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2405
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2573
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 107
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 196
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6059
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4538
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 54282
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 50577
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 31328
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 28826
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 25610
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 24118
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 23922
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 23719
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 54282
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 50577
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 31328
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 28826
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ኢሬቻ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ማንሰራራት!
Oct 3, 2025 585
ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ሰዎች በክረምት ወቅት ከሚከሰት መለያየትና መራራቅ በኋላ ዳግም የሚገናኙበት፣ በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት ዕለት ነው። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። ኢሬቻ የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ጥብቅ ቁርኝት የሚገለጽበት የገዳ ስርዓት አንዱ አካል ነው፡፡ የኢሬቻ እሴቶች ጠንካራ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ያላት ሀገር ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው። አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ አብሮነት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ዕርቅ እና ሌሎችም ተጠቃሽ የመልካም እሴቶች መገለጫ ነው። በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አንዱ እሴት ኢሬቻ ሲሆን፤ ለሀገር ማንሠራራትና ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሠረት ይሆናል፡፡ ኢሬቻ አብሮነት የሚጸናበት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ይበልጥ የሚጎላበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጎለብትበት፣ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ማሰሪያ ከፍ ያለ በዓል ነው፡፡ ኢሬቻ በጋራ የሚያከብሩትና የዓለም ቱሪስቶች የሚታደሙበት ሲሆን፤ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል አከባበር ሀገራዊ ማንሰራራት በተግባር የተረጋገጠበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ዓለም የኢትዮጵያን መቻል በተግባር ባየበትና ሌሎች ለሀገር ማንሰራራት ዕውን መሆን መሠረት የሚጥሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኘሮጀክቶች ይፋ በተደረጉበት ማግስት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡   በዓሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመላው ኢትዮጵያዊያንን ሕብረት የሚንጸባረቅበት ሆኖ በተለያዩ አከባቢዎች በድምቀት እየተከበረም ይገኛል፡፡ በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Waaqa Uumaa, Waaqa Uumamaa ፍጥረትን የፈጠርክ ፈጣሪ Gurraacha garaa garbaa የእውነትና የሰላም አምላክ! Dogoggora nu oolchi ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! Dacheef nagaa kenni ለምድራችን ሰላም ስጥ! Laggeenif nagaa kenni ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! Olota keenyaaf nagaa kenni ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! . . . Loowan keenyaaf nagaa kenni " ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "አሜን! አሜን! አሜን!” ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 25 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ " ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት " በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" Irreecha Birraa (በውኃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን፤ በዓመቱ አጋማሽ ላይ "ኢሬቻ ቱሉ" Irreecha Arfaasaa ደግሞ በተራራማ ቦታ ይከበራል። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ነው። የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመምጣቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ይህ ከማህበራዊ መስተጋብር አኳያም ሰዎች የሚሰባሰቡበትና የሚገናኙበት ነው። ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ብርሃን (ብራ) ስለደረሰ ለዚያ ምልክት ይሆን ዘንድ የለመለመ እርጥብ ሣር ይዘው ወደ ወንዝ በመውረድ ንጹህ ውሃ ውስጥ እየነከሩና እየረጩ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ አብሮነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። ኢሬቻ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው "ዋቃ" "Waaqa" ምስጋናውን ለማድረስ የሚከበር ሲሆን፤ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲከበር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። ኢሬቻ የወንድማማችነትና የአንድነት አርማ ሲሆን፤ የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ፣ የህብረ ብሔራዊ አብሮነት ማስተሳሰሪያም ጭምር ነው፡፡ በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይበዛል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል፣ አንድነት ይጸናል። ኢሬቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ነው። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ስለሆነም ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር እንዲህ እያሉ ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። የበዓሉ ታዳሚዎች ከዋዜማው ጀምሮ በሆረ ፊንፊኔና በሆረ ሀርሰዲ በመሰባሰብ፤ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎችን በማዜምና ምስጋና በማቅረብ አድረው በነጋታው ዋናውን የምስጋና በዓልም ያከናውናሉ፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የደስታና የምስጋና ምልክት የሆነውን ባህላዊ ነጫጭ ልብስ ለብሰው፣ ባህልን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ሁነቶችን በመከወን ልዩ ልዩ ዜማዎችን በማዜም፣ ግጥሞችን በማቅረብ፣ ወደ ፈጣሪ በመጸለይ እና ምስጋና በማቅረብ ሥርዓቱን ያከናውናሉ፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ከማቀራረብና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጾኦ ያለው ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገር የመጡ ልዑካን በበዓሉ ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። የኢሬቻ በዓል ለቱሪዝም ፍሰት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ጉልህ ነው፤ በርካታ የባህር ማዶ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የሚታደሙበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ ሲሆን፤ ዘርፉን በማጠናከር እና ብሔራዊ ልማትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚናንም የሚጫወት ነው፡፡ ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!        
በትግራይ ክልል የመስቀል በዓል አከባበር
Sep 27, 2025 681
የመስቀል በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በልዩ ድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ ነው። በዓሉ እንደየአካባቢው ባህላዊና ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል። በትግራይ ክልልም የመስቀል በዓል እንደሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሁሉ በናፍቆት ከሚጠበቁና በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት ተርታ ይመደባል። ለዚህም ሲባል የተለያዩ ዝግጅቶች ከበዓሉ ዋዜማ በፊት እንዲጠናቀቁ የሚደረግ ሲሆን፥ በተለይ በየዓመቱ መስከረም 16 እና 17 ዘመድ አዝማድ ተጠራርተው የሚገናኙበት የፍቅርና የአብሮነት በዓል ሆኖ ይከበራል። የክርስቶስ ግማደ መስቀል በንግስት ኢሌኒ አማካኝነት መገኘቱን በማሰብ በየዓመቱ መስከረም አጋማሽ ላይ የሚከበረው የመስቀል በዓል የመስቀል ኃያልነት፣ እውነት በተደበቀበት ለዘላለም እንደማይቀርና ፍቅርን አብዝቶ የሚሰበክበት ከዚህ ባለፈም እርቅ የሚወርድበትና ደስታ የሚገለጽበት አጋጣሚ መሆኑም ይገለጻል። በትግራይ የበዓሉን ታላቅነትና ክብር ለማድመቅ ምእመናን ጽዱ ልብስ ለብሰውና የተለያዩ ዝማሬዎችን በማሰማት ደመራ ወደሚደመርበት ሥፍራ ችቦ ይዘው በመሄድ ደምራውን በማቀጣጠል የሚያከበሩት ሲሆን፣ በእለቱ የቤት እንስሳት ጭምር ቀንዳቸውና ጀርባቸው ላይ ቅቤ ተቀብተው እንዲያርፉ ይደረጋል። ዘመድ አዝማድ፣ ጎረቤታሞች፣ አብሮ አደጎችና የበዓሉ ታዳሚ እንግዶችም ተሰባስበው ማለዳ ላይ ገንፎ በማዘጋጀት ይመገባሉ። የእንስሳት እርድ በማከናወን ባህላዊ መጠጦችን በማዘጋጀት በዓሉን የፍቅር፣ የመሰባሰብ፣ የአንድነትና ተካፍሎ የመብላት በዓል መሆኑን በተግባር የሚያሳይበት ክስተት ሆኖ ያልፋል። "ዓኾይ ዓኾኾይ" የጎመን ምንቸት ውጣ የገንፎ ምንቸት ግባ በማለትም ችቦ ተሎኮሶ በየቤቱ በመዞር የምረቃ እና ለሚቀጥለው ዓመትም በሰላምና ደስታ እንዲሁም እድሜና ጤናን በመመኘት ይከወናል። የአደባባይ በዓል የሆነው የመስቀል በዓል በዝማሬ፣ በሆታና እልልታ የሚገለጽ ሲሆን፤ ወርሃ መስከረም እሸት አሽቶ አበቦች አብበውና ምድር ልዩ ልምላሜን ተላብሶ የሚታይ በመሆኑ ልክ በታሪኩ እንደሰፈረው የሰላም፣ የእውነትና የአንድነት በዓል መሆኑን በተግባር የሚታይበት ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም