ቀጥታ፡

በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርን ከወንዝ ዳር ልማት ጋር በማስተሳሰር መጪው ትውልድን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ተግባራዊ ይደረጋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከወንዝ ዳር ልማት ጋር በማስተሳሰር መጪውን ትውልድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እስካሁን የተካሄዱ ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።


 

ከምልከታው በኋላም ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በክልሉ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ የተለያዩ ፍራፍሬ እና የደን ችግኞች ለተከላ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የሚተከሉ ችግኞችም በምግብ ራስን ለመቻል የሚያግዙ እና ለእንስሳት መኖነት የሚውሉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።


 

የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከወንዝ ዳር ልማት ጋር በማስተሳሰር መጪውን ትውልድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራም ነው የገለጹት።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም