ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት እየሰጠ ያለውን አገልግሎት ማጠናከር ይገባል
Nov 17, 2025 33
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት እየሰጠ ያለውን አገልግሎት አጠናክሮ መቀጣል እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎትን የ2018 ዓ.ም የአንደኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ገምግሟል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ባቀረቡት ሪፖርት እንዳሉት፤ በመጀመሪያው ሩብ አመት 545 ሺ 491 ፓስፖርት ለዜጎች ተደራሽ ተደርጓል። የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት (ኢ-ፓስፖርት) ደግሞ 14 ሺህ 818 ለሚሆኑ አገልግሎት ፈላጊዎች ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል። ከገቢ አኳያም በሩብ ዓመቱ 11 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ፤ በዚህም ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ማሰባሰብ መቻሉን አስረድተዋል። ሀሰተኛ ፓስፖርት ይዘው የተገኙ የአገር ውስጥና የውጪ ዜጎች በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉንም አብራርተዋል። በሩብ ዓመቱ 860 ሀሰተኛ ሰነድ ይዘው ፖስፖርት ለመውሰድ የሞከሩ የውጭ እና የአገር ውስጥ ዜጎች በቁጥጥር ስር ውለው በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉንም ገልጸዋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሯ ሰላማዊት ገለጻ፤ በሩብ ዓመቱ በድንበር አካባቢ በተከናወነ የቁጥጥር ሥራ 16 ሺህ 465 የሚሆኑ የውጭና የሀገር ውስጥ ዜጎች በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡና ከኢትዮጵያ ሊወጡ ሲሉ ተይዘዋል። በተቋሙ ሪፎርም ከተደረገ ወዲህ ከተገልጋዮች የሚነሱትን ጥያቄዎች በሟሟላት በመደበኛ በስድስት ወር ይሰጥ የነበረውን ፓስፖርት በሁለት ወራት እየተሰጠ መሆኑን አብራርተዋል። ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበርም ሕገ-ወጥነትን በመከላከል ዙሪያም የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ በበኩላቸው፤ አገልግሎቱ የዲጂታል አሰራር ሥርዓትን በመከተል መስጠት የጀመረውን አገልግሎት ይበልጥ ሊያጠናክር ይገባል። ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማቅረብ፣ ቅርንጫፎቹን ማስፋፋት እንዲሁም ተቋማዊ ደህንነት ለማጠናከር የጀመራቸውን ተግባራት ይበልጥ ማጠናክር እንደሚኖሩበትም አስገንዝበዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) በማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት፤ አገልግሎቱ ሕግን በማስከበር ላይ ውጤታማ ሥራ በማከናወኑ የሚበረታታ እና በጠንካራ ጎን የሚጠቀስ ነው። ሕገ-ወጥነትን መከላከል ላይ የጀመራቸውን ሥራዎች ማጠናከር እንዲሁም የድንበር አካባቢ ቁጥጥር ሥራዎችን በትኩረት መከወን እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመስጠት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል
Nov 17, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመስጠት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመርያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡ ሚኒስቴሩ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ፣ በዲጂታል መታወቂያና በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና አበረታች ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት ከተቋማት ጋር በመቀናጀት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ስራዎች በማከናወን ላይ ነው።   ቋሚ ኮሚቴው ሚኒስቴሩ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የመንግስትና የንግድ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል አስቻይ ሁኔታ በመፍጠር ሀገራዊ ኢ-ኮሜርስና የኢንተርኔት የንግድ ግብይት ስርዓትን ለማሳደግ ምን እየሰራ እንደሆነ ጥያቄ አቅርቧል። የኢትዮ-ኮደርስ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ስልጠና ለመስጠት የሚኒስቴሩ ድጋፍና ክትትል ምን ይመስላል በሚለው ላይም ማብራሪያ ጠይቋል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) የተቋማቸውን አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት እንዳስታወቁት፤ ባለፉት ሶስት ወራት በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል፡፡ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ከተቋማት ጋር በመቀናጀት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ስራዎች መከናወናቸውን በመግለጽ። በዚህም 10 የንግድ ተቋማት ወደ ኤሌክትሮኒክ ግብይት መግባታቸውን፣ ሶስት የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማሳለጫ ፕላት ፎርሞችን በማዘጋጀት ለ56 አይሲቲና ዲጂታል ኢንዱስትሪዎች ብቃት ማረጋገጫ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።   በሌላ በኩል በኦንላይን የሚሰጡ የመንግስት አገልግሎቶችን በሚመለከት የተያዘውን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ማሳካት መቻሉንም አስታውቀዋል። ከዲጂታል መታወቂያ ጋር በተያያዘ በ2018 የመጀመርያ ሩብ ዓመት አምስት ሚሊዮን ተጠቃሚዎች አገልግሎቱን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል። በኢትዮ-ኮደርስ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ስልጠና ባለፉት ሶስት ወራት ከ ሁለት ነጥብ አራት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው ሚኒስትር ዴኤታው ያነሱት። ከተሞችን በዲጂታል አድራሻ ስርዓት ለማካተት በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰው፤ በሩብ ዓመቱ የአምስት ከተሞች ትግበራን የማጠናቀቅ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። ሀገራዊ ኢኖቬሽን ምርምርና ቴክኖሎጂን በሚመለከት በሩብ ዓመቱ ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ነው ያስታወቁት፡፡   እንዲሁም 205 ችግር ፈቺ ምርምሮችን በምርምር እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማከናወን መቻሉንም አንስተዋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፤ ሚኒስቴሩ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ የተቋማትንና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል። የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አበረታች መሆኑን ጠቅሰው፤ ተቋማት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት እንዲሰጡ በቅንጅት መስራት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ኢንዱስትሪ ለመሸጋገር በምታደርገው ጉዞ ቴክኖሎጂ አስፈላጊ በመሆኑ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር የሚደረገው ቅንጅታዊ አሰራር ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት። ተቋማት ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለመጠቀም ዝግጁ እንዲሆኑ ማገዝ እንደሚገባ አሳስበው፤ ቴክኖሎጂውን አስመልክቶ ለተቋማትና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶር) በመጨረሻም በቋሚ ኮሚቴው የተነሱ ክፍተቶችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በትኩረት እንሰራለን ሲሉ አረጋግጠዋል፡፡
ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በአዲስ አበባ ይካሄዳል 
Nov 17, 2025 36
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡- የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል ይደረጋል። የሽልማት ስነ ስርዓት “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶ ግራፈር፣ ሀገር በቀል/ ብሄራዊ ቋንቋ ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ከእ.አ.አ 2023 ጀምሮ እየተካሄደ የሚገኝ ዓመታዊ ሁነት ነው። የ2023 ሽልማት በጅቡቲ፣ የ2024ቱ በኬንያ ናይሮቢ መካሄዱ ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የደረሰችበትን እድገት የሚየሳዩ እና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች እየተገነቡ ነው - ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ
Nov 17, 2025 35
ባህር ዳር፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የደረሰችበትን እድገት የሚያሳዩ እና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች እየተገነቡ መሆኑን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ አስታወቁ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና ማሕበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የባሕር ዳር ስታዲየምንና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩትን ተመልክተዋል።   የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በሀገሪቱ የስፖርት ልማት፣ ውጤታማነትን በሚያረጋግጥ አግባብ እየተከናወነ ነው። ከለውጡ ወዲህ ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች አንዱ የስፖርት ልማት መሆኑን ጠቅሰው፤ ለዚህም ጥናት ላይ የተመሰረተ ስትራቴጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ ይገኛል ብለዋል። በተለይም ህፃናትና ታዳጊዎች ላይ በመመስረት ተተኪና ብቃት ያላቸው ስፖርተኞችን በሁሉም ዘርፎች ማፍራት የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳዎችን ችግር በመፍታት ውጤታማ ስራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በመላ ሀገሪቱ በርካታ መካከለኛና አነስተኛ ስታዲየሞች መገንባት ተችሏል ብለዋል።   እንዲሁም ነባርና አዳዲስ ታላላቅ ስታዲየሞች ግንባታ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን በጠበቀ አግባብ እየተገነቡ መሆኑን ጠቁመው መንግስት ዘርፉን ለማሳደግ ልዩ ትኩረት በመስጠት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሰስ እያደረገ ይገኛል ነው ያሉት። የባህር ዳር፣ ድሬዳዋ፣ አርባ ምንጭ፣ አደይ አበባ እና ሌሎች ታላላቅ ስታዲየሞች የፊፋንና ካፍን ደረጃ በጠበቀ መንገድ እየተገነቡ መሆኑን ጠቅሰው ከፍተኛ ክትትል እየተደረገባቸው በሙያ ታግዘው እየተሰሩ ነው ብለዋል። አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በቀጣይ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ስሟ ከፍ ብሎ እንዲጠራ የሚያስችሉ ብቃት ያላቸው ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል። መንግስት ለስፖርት ልማት ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱንና እየተገነቡ ያሉ ስታዲየሞች የኢትዮጵያን ገፅታና እድገት በሚያሳይ አግባብና ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።   በኢትዮጵያ የስፖርት ልማት ዘርፍ የህዝብ ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጥ መንገድ እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና ማሕበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ(ዶ/ር ) ናቸው። ስፖርት ለኢኮኖሚ እድገት ካለው ፋይዳ ባሻገር ማህበረሰቡ በትርፍ ጊዜው መዝናናት እንዲችል ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ ይገኛል ብለዋል። የባህር ዳር ስታዲየም ግንባታ ዓለም አቀፍ መስፈርት ባሟላ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን ማረጋገጥ እንደተቻለ ጠቅሰው፤ በቀጣይ የስታዲየሙ ጥላ በትብብር የሚሰራበትን ሁኔታ ስራ አስፈፃሚው ሊያመቻች ይገባል ነው ያሉት። አሁን ላይ ስፖርት ጨዋታ ብቻ አይደለም ያሉት ምክትል ሰብሳቢው ስፖርት የሀገር ሉዓላዊነት፣ ዲፕሎማሲ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ መስተጋብርና ሌሎች ሁሉን አቀፍ ጉዳዮችን የያዘ መሆኑንም ገልጸዋል። በዘርፉ እየተከናወኑ የሚገኙ ልማቶች የበለጠ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውና ለዚህም ምክር ቤቱ ተገቢውን እገዛና ክትትል እንደሚያደርግ ተናግረዋል።   የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሕዝብ ግንኙነት አማካሪ እርዚቅ ኢሣ በበኩላቸው፤ የባሕር ዳር ስታዲየም የካፍና ፊፋ መስፈርቶችን መሰረት በማድረግ እየተገነባ መሆኑን ጠቁመው ትላልቅ ጨዋታዎችን ማስተናገድ እንዲችል ሆኖ በጥራት እየተሰራ ነው ብለዋል። ለስታዲየሙ የሚያስፈልገው የመጠለያ ስራም በቀጣይ የክልሉና የፌደራል መንግስት በትብብር እንደሚሰሩበት ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች ተተግብረዋል - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
Nov 17, 2025 71
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች መተግበራቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጠባቂነትን አስወግዶ በሀሳብ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል ያሳየ ተቋም መሆኑንም ጠቅሰዋል። የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴርና ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ተከፍቷል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር)፣ ዲፕሎማቶችና ሌሎች ተሳታፊዎች በመክፈቻ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተዋል። ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ስሟን ከፍ ያደረጉ አንቱ የተባሉ ምስጉን፣ ታታሪ ኢንተርፕርነሮችስ ስትፈጥር ቆይታለች።   ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስቷ መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትን የገነባችው፣ ሕጎችን ያወጣችው ባለፉት ሰባት ዓመታት ነው ብለዋል። በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት የኢንተርፕርነርሽፕ ሥነ ምህዳርን ተቋማዊ ማድረግ የሚያስችል እንቅስቃሴ መደረጉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የሀሳብ ብዝሃነት ጸጋ ለሀሳብ ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጠባቂነትን አስወግዶ በሀሳብ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል በተግባር አሳይቷል ነው ያሉት። በዚህም ባለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች ተተግብረዋል ብለዋል። ኢትዮጵያ የኢንተርፕርነሮች መፍለቂያ ትሆናለች ያሉት ሚኒስትሯ፤ መንግሥት የኢንተርፕርነርሽፕ ምህዳሩን ምቹ ማድረጉን ገልጸዋል። ሀሳብ ካለ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል አምናለሁ ያሉት ሚኒስትሯ፤ ይህን ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል እምቅ ሀገራዊ አቅም፣ ፖሊሲና ተቋም ተገንብቷልም ብለዋል። የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያ ኢንተርፕርነር መሆንና እንዴት እንደምትሆን በግልጽ አስቀምጧል ነው ያሉት።   የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሽፕ ሁነቶችን በማዘጋጀት ብራዚልን በመቅደም ከዓለም አንደኛ ሆናለች ብለዋል። ኢንተርፕርነሮች የፈጠራ መፍትሔዎችን ወደ መሬት የሚቀይሩ፣ ምኞትን የሚያሳኩ፣ አይቻልምን ችለው የሚያሳዩ ፈር ቀዳጅ ባለራዕዮችና ከዋኞች ናቸው ነው ያሉት። ኢንተርፕርነሮች ሀገር ሰሪዎች መሆናቸውን ጠቁመውም በዘንድሮው 12ኛው የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ስልጠናዎች፣ የፈጠራ ሀሳብ ውድድሮችና ጥናቶች ይከናወናሉ ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚወሰን ሳይሆን ድንበር ተሻጋሪ ሥራ ጀምረናል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የመጨረሻ ግባችን አይበገሬ ማህበረሰብ፣ ዜጋና ሀገር መገንባት ነው ሲሉም ገልጸዋል።
የሚታይ
የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመስጠት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል
Nov 17, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመስጠት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመርያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡ ሚኒስቴሩ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ፣ በዲጂታል መታወቂያና በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና አበረታች ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት ከተቋማት ጋር በመቀናጀት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ስራዎች በማከናወን ላይ ነው።   ቋሚ ኮሚቴው ሚኒስቴሩ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የመንግስትና የንግድ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል አስቻይ ሁኔታ በመፍጠር ሀገራዊ ኢ-ኮሜርስና የኢንተርኔት የንግድ ግብይት ስርዓትን ለማሳደግ ምን እየሰራ እንደሆነ ጥያቄ አቅርቧል። የኢትዮ-ኮደርስ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ስልጠና ለመስጠት የሚኒስቴሩ ድጋፍና ክትትል ምን ይመስላል በሚለው ላይም ማብራሪያ ጠይቋል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) የተቋማቸውን አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት እንዳስታወቁት፤ ባለፉት ሶስት ወራት በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል፡፡ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ከተቋማት ጋር በመቀናጀት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ስራዎች መከናወናቸውን በመግለጽ። በዚህም 10 የንግድ ተቋማት ወደ ኤሌክትሮኒክ ግብይት መግባታቸውን፣ ሶስት የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማሳለጫ ፕላት ፎርሞችን በማዘጋጀት ለ56 አይሲቲና ዲጂታል ኢንዱስትሪዎች ብቃት ማረጋገጫ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።   በሌላ በኩል በኦንላይን የሚሰጡ የመንግስት አገልግሎቶችን በሚመለከት የተያዘውን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ማሳካት መቻሉንም አስታውቀዋል። ከዲጂታል መታወቂያ ጋር በተያያዘ በ2018 የመጀመርያ ሩብ ዓመት አምስት ሚሊዮን ተጠቃሚዎች አገልግሎቱን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል። በኢትዮ-ኮደርስ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ስልጠና ባለፉት ሶስት ወራት ከ ሁለት ነጥብ አራት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው ሚኒስትር ዴኤታው ያነሱት። ከተሞችን በዲጂታል አድራሻ ስርዓት ለማካተት በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰው፤ በሩብ ዓመቱ የአምስት ከተሞች ትግበራን የማጠናቀቅ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። ሀገራዊ ኢኖቬሽን ምርምርና ቴክኖሎጂን በሚመለከት በሩብ ዓመቱ ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ነው ያስታወቁት፡፡   እንዲሁም 205 ችግር ፈቺ ምርምሮችን በምርምር እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማከናወን መቻሉንም አንስተዋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፤ ሚኒስቴሩ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ የተቋማትንና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል። የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አበረታች መሆኑን ጠቅሰው፤ ተቋማት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት እንዲሰጡ በቅንጅት መስራት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ኢንዱስትሪ ለመሸጋገር በምታደርገው ጉዞ ቴክኖሎጂ አስፈላጊ በመሆኑ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር የሚደረገው ቅንጅታዊ አሰራር ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት። ተቋማት ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለመጠቀም ዝግጁ እንዲሆኑ ማገዝ እንደሚገባ አሳስበው፤ ቴክኖሎጂውን አስመልክቶ ለተቋማትና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶር) በመጨረሻም በቋሚ ኮሚቴው የተነሱ ክፍተቶችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በትኩረት እንሰራለን ሲሉ አረጋግጠዋል፡፡
ኢትዮጵያ የደረሰችበትን እድገት የሚየሳዩ እና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች እየተገነቡ ነው - ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ
Nov 17, 2025 35
ባህር ዳር፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የደረሰችበትን እድገት የሚያሳዩ እና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች እየተገነቡ መሆኑን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ አስታወቁ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና ማሕበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የባሕር ዳር ስታዲየምንና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩትን ተመልክተዋል።   የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በሀገሪቱ የስፖርት ልማት፣ ውጤታማነትን በሚያረጋግጥ አግባብ እየተከናወነ ነው። ከለውጡ ወዲህ ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች አንዱ የስፖርት ልማት መሆኑን ጠቅሰው፤ ለዚህም ጥናት ላይ የተመሰረተ ስትራቴጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ ይገኛል ብለዋል። በተለይም ህፃናትና ታዳጊዎች ላይ በመመስረት ተተኪና ብቃት ያላቸው ስፖርተኞችን በሁሉም ዘርፎች ማፍራት የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳዎችን ችግር በመፍታት ውጤታማ ስራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በመላ ሀገሪቱ በርካታ መካከለኛና አነስተኛ ስታዲየሞች መገንባት ተችሏል ብለዋል።   እንዲሁም ነባርና አዳዲስ ታላላቅ ስታዲየሞች ግንባታ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን በጠበቀ አግባብ እየተገነቡ መሆኑን ጠቁመው መንግስት ዘርፉን ለማሳደግ ልዩ ትኩረት በመስጠት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሰስ እያደረገ ይገኛል ነው ያሉት። የባህር ዳር፣ ድሬዳዋ፣ አርባ ምንጭ፣ አደይ አበባ እና ሌሎች ታላላቅ ስታዲየሞች የፊፋንና ካፍን ደረጃ በጠበቀ መንገድ እየተገነቡ መሆኑን ጠቅሰው ከፍተኛ ክትትል እየተደረገባቸው በሙያ ታግዘው እየተሰሩ ነው ብለዋል። አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በቀጣይ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ስሟ ከፍ ብሎ እንዲጠራ የሚያስችሉ ብቃት ያላቸው ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል። መንግስት ለስፖርት ልማት ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱንና እየተገነቡ ያሉ ስታዲየሞች የኢትዮጵያን ገፅታና እድገት በሚያሳይ አግባብና ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።   በኢትዮጵያ የስፖርት ልማት ዘርፍ የህዝብ ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጥ መንገድ እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና ማሕበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ(ዶ/ር ) ናቸው። ስፖርት ለኢኮኖሚ እድገት ካለው ፋይዳ ባሻገር ማህበረሰቡ በትርፍ ጊዜው መዝናናት እንዲችል ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ ይገኛል ብለዋል። የባህር ዳር ስታዲየም ግንባታ ዓለም አቀፍ መስፈርት ባሟላ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን ማረጋገጥ እንደተቻለ ጠቅሰው፤ በቀጣይ የስታዲየሙ ጥላ በትብብር የሚሰራበትን ሁኔታ ስራ አስፈፃሚው ሊያመቻች ይገባል ነው ያሉት። አሁን ላይ ስፖርት ጨዋታ ብቻ አይደለም ያሉት ምክትል ሰብሳቢው ስፖርት የሀገር ሉዓላዊነት፣ ዲፕሎማሲ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ መስተጋብርና ሌሎች ሁሉን አቀፍ ጉዳዮችን የያዘ መሆኑንም ገልጸዋል። በዘርፉ እየተከናወኑ የሚገኙ ልማቶች የበለጠ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውና ለዚህም ምክር ቤቱ ተገቢውን እገዛና ክትትል እንደሚያደርግ ተናግረዋል።   የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሕዝብ ግንኙነት አማካሪ እርዚቅ ኢሣ በበኩላቸው፤ የባሕር ዳር ስታዲየም የካፍና ፊፋ መስፈርቶችን መሰረት በማድረግ እየተገነባ መሆኑን ጠቁመው ትላልቅ ጨዋታዎችን ማስተናገድ እንዲችል ሆኖ በጥራት እየተሰራ ነው ብለዋል። ለስታዲየሙ የሚያስፈልገው የመጠለያ ስራም በቀጣይ የክልሉና የፌደራል መንግስት በትብብር እንደሚሰሩበት ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች ተተግብረዋል - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
Nov 17, 2025 71
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች መተግበራቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጠባቂነትን አስወግዶ በሀሳብ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል ያሳየ ተቋም መሆኑንም ጠቅሰዋል። የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴርና ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ተከፍቷል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር)፣ ዲፕሎማቶችና ሌሎች ተሳታፊዎች በመክፈቻ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተዋል። ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ስሟን ከፍ ያደረጉ አንቱ የተባሉ ምስጉን፣ ታታሪ ኢንተርፕርነሮችስ ስትፈጥር ቆይታለች።   ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስቷ መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትን የገነባችው፣ ሕጎችን ያወጣችው ባለፉት ሰባት ዓመታት ነው ብለዋል። በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት የኢንተርፕርነርሽፕ ሥነ ምህዳርን ተቋማዊ ማድረግ የሚያስችል እንቅስቃሴ መደረጉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የሀሳብ ብዝሃነት ጸጋ ለሀሳብ ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጠባቂነትን አስወግዶ በሀሳብ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል በተግባር አሳይቷል ነው ያሉት። በዚህም ባለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች ተተግብረዋል ብለዋል። ኢትዮጵያ የኢንተርፕርነሮች መፍለቂያ ትሆናለች ያሉት ሚኒስትሯ፤ መንግሥት የኢንተርፕርነርሽፕ ምህዳሩን ምቹ ማድረጉን ገልጸዋል። ሀሳብ ካለ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል አምናለሁ ያሉት ሚኒስትሯ፤ ይህን ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል እምቅ ሀገራዊ አቅም፣ ፖሊሲና ተቋም ተገንብቷልም ብለዋል። የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያ ኢንተርፕርነር መሆንና እንዴት እንደምትሆን በግልጽ አስቀምጧል ነው ያሉት።   የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሽፕ ሁነቶችን በማዘጋጀት ብራዚልን በመቅደም ከዓለም አንደኛ ሆናለች ብለዋል። ኢንተርፕርነሮች የፈጠራ መፍትሔዎችን ወደ መሬት የሚቀይሩ፣ ምኞትን የሚያሳኩ፣ አይቻልምን ችለው የሚያሳዩ ፈር ቀዳጅ ባለራዕዮችና ከዋኞች ናቸው ነው ያሉት። ኢንተርፕርነሮች ሀገር ሰሪዎች መሆናቸውን ጠቁመውም በዘንድሮው 12ኛው የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ስልጠናዎች፣ የፈጠራ ሀሳብ ውድድሮችና ጥናቶች ይከናወናሉ ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚወሰን ሳይሆን ድንበር ተሻጋሪ ሥራ ጀምረናል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የመጨረሻ ግባችን አይበገሬ ማህበረሰብ፣ ዜጋና ሀገር መገንባት ነው ሲሉም ገልጸዋል።
የፀጥታ ሀይሉ የጋምቤላ ክልል ሰላምና ፀጥታን አስተማማኝ በማድረግ ልማትና ብልጽግና እንዲፋጠን አድርጓል - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Nov 17, 2025 51
ጋምቤላ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የፀጥታ ሀይሉ የጋምቤላ ክልልን ሰላምና ፀጥታን አስተማማኝ በማድረግ ልማትና ብልጽግና እንዲፋጠን ማድረጉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። “ከጂኦስትራቴጂካዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና” በሚል መሪ ሀሳብ የክልሉን የፀጥታ ሀይል ሙያዊ እውቀትና ክህሎት የሚያሳድግ የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ በጋምቤላ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የህዝቡን ሰላምና ፀጥታ በማስጠበቅ ለክልሉ የልማትና መልካም አስተዳደር ግብ መሳካት የጸጥታ አካላት ሚና የላቀ ነው።   የክልሉ ፖሊስ የክልሉን ሰላም ለማጽናትና ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን የውስጥና ድንበር ተሻጋሪ የፀረ ሰላም እንቅስቃሴዎችን በመከላከል ረገድ ያለው ኃላፊነት ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም የፀጥታ አካላትን በእውቀት፣ በክህሎትና በስነ-ልቦና በመገንባት ኃላፊነታቸውን የበለጠ እንዲወጡ የአቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። በዕለቱ የተጀመረው የአቅም ግንባታ ስልጠና የፀጥታ አካላቱ ዘመናዊ የውትድርና ሳይንሱን በመያዝ ለክልሉም ሆነ ለሀገር ሰላምና ብሔራዊ ጥቅም መከበር ከመቼውም ግዜ በላይ እንዲተጉ አቅማቸውን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።   የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ኡጉላ ኡጁሉ በበኩላቸው ኮሚሽኑ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ በማስጠበቅ ረገድ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ለክልሉ የፀጥታ አመራሮችና ለአባላት እየተሰጠ ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና አለም አቀፍ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ጉዳዮችን ተረድቶ ኃላፊነቱን በብቃትና በአሸናፊነት መንፈስ የሚወጣ ሃይል ለማፍራት መሆኑን ተናግረዋል። በዕለቱ በተጀመረው የአቅም ግንባታ ስልጠና ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የፀጥታ አመራሮችና አባላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
በክልሉ ጠንካራ የፖሊስ ተቋምና አመራር ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት -ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Nov 17, 2025 47
ባህርዳር፤ ህዳር 8/2018 (ኢዜአ)፦ በክልሉ ጠንካራ የፖሊስ ተቋምና አመራር ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የአማራ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ “ከጂኦ ስትራቴጂክ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሃሳብ ለከፍተኛና መካከለኛ የፖሊስ አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እያካሄደ ይገኛል። ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ እንደገለጹት፤ ጂኦ ስትራቴጂ የሚያስገኘውን ጥቅምና ተግዳሮት ላይ ለሁሉም ህብረተሰብ ሰፊ ግንዛቤ ለመፍጠር እየተሰራ ነው።   ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር በቅርበት የምትገኝና የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ባለቤት በመሆኗ ከአለም ማህበረሰብ በእጅጉ የተሳሰረ የጂኦስትራቴጂ እድልና ተግዳሮት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም አገራችን ያወጣችውን የጂኦስትራቴጂ ፖሊሲና እቅድ በአግባቡ በመምራት ያለንን እድል ወደ ድል በመቀየር ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን ማስጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው ብለዋል። ፖሊስ ወንጀልን በመከላከልና የክልሉን ሰላም በማፅናት ለብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ብለዋል። በክልሉ ጠንካራ የፖሊስ ተቋምና አመራር ለመገንባት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀው፤ ይህም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመልክተዋል። የፖሊስ አመራሩና አባሉ ጂኦስትራቴጂ የሚያስገኘውን ጥቅም፣ ሊያጋጥም የሚችለውን ተግዳሮትና የአለምን ነባራዊ ሁኔታ በአግባቡ በመገንዘብ ራሱን ለተልዕኮ ዝግጁ ማድረግ እንደሚገባው ገልጸዋል።   የአማራ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የሚሰጠው ስልጠና የፖሊስ አመራሩን ለላቀ ተልዕኮ ለማዘጋጀት የሚያስችል ነው ብለዋል። በዚህም የክልሉን ወቅታዊና ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብና ሰላምን ለማጠናከር የበኩላችንን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችል መሆኑን ተገንዝቦ ስልጠናውን በአግባቡ መከታተል ይገባል ብለዋል። በስልጠናው ላይ የክልሉ፣ የሰሜን ጎጃም ዞንና የባህርዳር ከተማ አስተዳደር የፖሊስ አመራሮች መሳተፋቸውም ተመላክቷል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር በጋራ መልማትና መስራትን በማንበር ትስስርን አጠናክሯል
Nov 17, 2025 58
ሰመራ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል መከበር በጋራ መልማትና መስራትን በማንበር ትስስርን ማጠናከር መቻሉን የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ አሲያ ከማል ተናገሩ። 20ኛውን የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሐሳብ የአፋርና የአማራ ክልሎች አጎራባች ዞኖች በጋራ በመሆን በአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ አክብረዋል። በዓሉ የተከበረው የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ እና የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ አሲያ ከማልን ጨምሮ የአርጎባ እና ዱለቻ ወረዳ ነዋሪዎች በተገኙበት ነው። የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አሲያ ከማል በዚሁ ወቅት እንደገለፁት የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል መከበር ብሔሮችና ብሔረሰቦች የጋራ የሆኑ እሴቶች እንዲያጠናክሩ እያገዘ ነው። በዓሉ የጋራ እሴቶችን በማጎልበት ክልሎች በአንድ ላይ ሆነው በመስራትና በልማት ግንኙነታቸውን ማጠናከር መቻሉን ተናግረዋል። የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በማጎልበት በአጎራባች ዞኖችና ወረዳዎች ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ዳብሮ በልማታዊ ስራዎች መደጋገፋቸው ተጠናክሯልም ብለዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ በበኩላቸው የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አብሮነትን በማጠናከር ለትብብር የጎላ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። የጋራ ትርክቶችን በማሰረፅ ረገድም በዓሉ ሚናው ከፍተኛ ነው ብለዋል። እጅ ለእጅ ተያይዘን በአንድነት መጓዝ እንደምንችልና የተጋመደውን ወንድማማችነት እና እህትማማችነት በስራና አብሮ በመልማት ማጠናከር ይገባናል ሲሉም ተናግረዋል።      
በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 17, 2025 58
ድሬዳዋ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ከሪማ አሊ ተናገሩ። የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች እና አመራሮች 20ኛውን የብሔሮች -ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በፓናል ውይይት አክብረዋል። በመድረኩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈጉባ ከሪማ አሊ፤ የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ስናከብር በየአካባቢው ያልተገለጡ እሴቶችን በማስተዋወቅና በመጋራት እንዲሁም ለሀገር ልማትና ብልጽግና በጋራ በመትጋት መሆን አለበት ብለዋል። ዘንድሮም ለልማት በመትጋትና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት ማክበር እንዳለበት አንስተዋል።   በመሆኑም የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫና የፍቅር ምልክት በሆነችው ድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት።   የድሬዳዋ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ሐይር ሐጂ ኑር፤ የበዓሉ መከበር ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት የተጀመሩ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማሳካት በጋራ ለመትጋት መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸው ለውጤታማነት ቅንና ፍትሃዊ አገልጋይ በመሆን መስራት አለብን ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችም በቅንነትና በታማኝነት ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ለለውጥና ማንሰራራት እንሰራለን ነው ያሉት።
 የፖሊስ ተቋምን በማዘመን የሰላምና ልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ይሰራል
Nov 17, 2025 63
ሆሳዕና፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖሊስ ተቋምን ከወቅቱ ጋር በማዘመን የሰላምና ልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ይሰራል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ። በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን "ከጂኦስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሀሳብ ለፖሊስ አመራሮችና አባላት ያዘጋጀው ስልጠና በሆሳዕና ከተማ እየተሰጠ ነው፡፡   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት፤ ፖሊስ ጸጥታና ደህንነትን በማስጠበቅ የክልሉ ሰላምና ልማት እንዲጠናከር አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ፖሊስ ከማህበረሰቡ ጋር የቅርብ ቁርኝት ያለው መሆኑን አስታውሰው ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባና በየአካባቢው ልማት እንዲፋጠን ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።   የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በማፋጠን የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰላምና ደህንነት አጠናክሮ ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ፖሊስ ይህን ሀላፊነቱን በላቅ ብቃት እንዲወጣ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። ለዚህም አሰራሩን ወቅቱን በሚመጥን መልኩ የማዘመን ሥራ እንደሚሰራና የፖሊስ አባላትን አቅም በተለያየ መንገድ የመገንባት ሥራም ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል።
በዓሉ ብዝሃነትን ለማስረጽ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Nov 17, 2025 89
አሶሳ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ብዝሃነትን ለማስረጽ እና አንድነትን ለማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አስካለች አልቦሮ ገለጹ፡፡ አፈ ጉባኤዋ በሰጡት መግለጫ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር አስታውቀዋል። በዓሉ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በስፖርታዊ ውድድሮች፣ በጥያቄና መልስ እንዲሁም ብዝሃነትን በሚያንፀባርቁ ሁነቶች እንደሚከበር ጠቁመዋል። በዓሉ በክልሉ ደረጃ በካማሽ ዞን ካማሽ ከተማ እንደሚከበር የገለፁት አፈ ጉባኤዋ፤ በበዓሉ ላይ ከክልሉ በተጨማሪ የአጎራባች ክልሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ ብለዋል። የካማሽ ዞን ከነበረበት የፀጥታ ችግር ተላቆ በተለያዩ የልማት ስራዎች አመርቂ ውጤቶችን እያሳየ በመሆኑ በዓሉ የዞኑን አሁናዊ ሁኔታ ለሌሎች አካባቢዎች ለማሳየት እንደሚያግዝ ተናግረዋል። የካማሽ ዞን በዓሉን ለማስተናገድ እና እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት መጀመሩንም አፈ ጉባኤዋ ገልጸዋል። የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል በህዝቦች መካከል ያለውን አብሮነት በማጠናከርና ሀገራዊ ትርክት ለመገንባት የሚያግዝ መሆኑን አስታውቀዋል።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የእጩ ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል
Nov 17, 2025 88
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የእጩ ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የግል ዕጩዎች ምዝገባ የሚጀመርበት ጊዜ በቀጣይ ይፋ እንደሚሆንም ጠቁሟል። ምርጫ ቦርድ በጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ባደረገው ጥሪ እጩዎቻቸውን ቦርዱ በገለጸው ሲስተም ተጠቅመው እንደሚያስመዘግቡ ጥሪ አቅርቧል። ምዝገባውን ለማከናወን የሚያስችሉ አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ከህዳር 8 እስከ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በቦርዱ ዋና መሥሪያ ቤት እና ከዚህ ቀደም ፓርቲው ለቦርዱ ባሳወቀው/ባሳወቃት ወኪል አማካኝነት በአካል በመገኘት ሠነዱን እንዲያቀርቡ አሳስቧል። ፖለቲካ ፓርቲዎቹ ቅጾቹን ከ https://nebe.org.et/en/node/725 ላይ ማግኘት እንደሚችሉም ጠቁሟል። በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ለውድድር የተጠቀሙባቸው መወዳደሪያ ምልክቶችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጠቀም ቀዳሚ መብት እንዳላቸው ቦርዱ ገልጿል። ፖለቲካ ፓርቲዎች የሕጉን መሥፈርት የተከተለ የራሳቸውን የመወዳደሪያ ምልክት ማቅረብ እንደሚችሉና በአማራጭነት ቦርዱ ጋር በአካል በመቅረብ ቦርዱ ከሚያቀርበው የመወዳደሪያ ምልክት ዝርዝር ውስጥ መምረጥ እንደሚችሉም አመልክቷል። የግል ዕጩዎች ምዝገባ ቦርዱ በገለጸው መተግበሪያ እንደሚያከናውንና የሚጀመርበትን ጊዜ በተመለከተ ቦርዱ በቀጣይ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የልማት ስራዎች ከዳር እንዲደርሱ የፖሊስ አባላት ሚና ሊጠናከር ይገባል
Nov 17, 2025 54
ቦንጋ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-የተወጠኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶችና ሌሎች የልማት ስራዎች ከግብ እንዲደርሱ የፖሊስ አባላት ያለባቸውን ኃላፊነትና ሚና ሊያጠናክሩ ይገባል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አሳሰቡ። "ከጂኦ ስትራቴጂካዊ ኩስመና ወይ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሃሳብ ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ የፖሊስ አመራሮችና አባላት የተዘጋጀ ስልጠና በቦንጋ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።   የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ እንደገለፁት፣ ከለውጡ ወዲህ በርካታ ፈተናዎች ውስጥ በማለፍ በርካታ ድሎችን ማስመዝገብ ተችሏል። ለውጡ ብዙ መስዋእትነት የተከፈለበት መሆኑን ጠቅሰው የፖሊስ አባላቱ ከዚህ ቀደም ከነበረው የበለጠ ትጋትና ቁርጠኝነት እንዲሁም ጀግንነት የሚጠይቁ ተግባራት ከፊታቸው እንዳሉ ሊገነዘቡ እንደሚገባም አንስተዋል። ስለሆነም በመንግስት የተወጠኑ የልማት ስራዎች ከዳር እንዲደርሱ የፖሊስ አባላት ኃላፊነትና ሚና ሊጠናከር ይገባል ብለዋል። የፖሊስ አባሉ አሁን ያለውን ክልላዊ፣ ሀገር አቀፋዊና ቀጠናዊ ሁኔታዎችን በተገቢው ለማወቅና ለመረዳት የሚያስችለው ስልጠና መሆኑን አፈ-ጉባኤው አስረድተዋል። የክልሉ ሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ዓለሙ፤ ስልጠናው የዓለም-አቀፉን የጂኦ ፖለቲካ ሁኔታ በመገንዘብ ተገቢውን ቁመና ለመያዝና የፖሊስ ሠራዊቱን አረዳድ የተሻለ ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።   ስልጠናው ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥም ታውቋል።
የክልሉ ፖሊስ ሕግን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ ነው
Nov 17, 2025 84
አሶሳ፤ ሕዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት እያስጠበቀ የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ "ከጂኦስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሐሳብ ለክልሉ ፖሊስ እና ፀጥታ አካላት የሚሰጠውን ስልጠና አስጀምረዋል።   በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን እንደተናገሩት፤ የፀጥታ አካላት ዋነኛው ተልዕኮ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅና ሕግ ማስከበር ነው። ተለዋዋጭ የሆነውን ወቅታዊ ጂኦፖለቲክስ በመረዳት እና በተደመረ አቅም የክልሉን ሰላም ለመጠበቅ የሚያግዝ የፀጥታ ሀይል እንዲኖር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።   ከዚህ ባለፈ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ሀገሪቷ የምታከናውናቸው ግዙፍ የልማት እንቅስቃሴዎች ደህንነት ማስጠበቅ እንዳለባቸውም አሳስበዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ሀሩን ዑመር በበኩላቸው፤ ስልጠናው በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የፖሊስ አባላት ተቀራራቢ ግንዛቤ እንዲኖራቸው እና ለላቀ ተልዕኮ ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።   ለሁለት ቀናት በተሰናዳው ስልጠና ላይ የክልሉ የፖሊስ አመራሮች እና አባላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ፖለቲካ
የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር በጋራ መልማትና መስራትን በማንበር ትስስርን አጠናክሯል
Nov 17, 2025 58
ሰመራ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል መከበር በጋራ መልማትና መስራትን በማንበር ትስስርን ማጠናከር መቻሉን የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ አሲያ ከማል ተናገሩ። 20ኛውን የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሐሳብ የአፋርና የአማራ ክልሎች አጎራባች ዞኖች በጋራ በመሆን በአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ አክብረዋል። በዓሉ የተከበረው የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ እና የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ አሲያ ከማልን ጨምሮ የአርጎባ እና ዱለቻ ወረዳ ነዋሪዎች በተገኙበት ነው። የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አሲያ ከማል በዚሁ ወቅት እንደገለፁት የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል መከበር ብሔሮችና ብሔረሰቦች የጋራ የሆኑ እሴቶች እንዲያጠናክሩ እያገዘ ነው። በዓሉ የጋራ እሴቶችን በማጎልበት ክልሎች በአንድ ላይ ሆነው በመስራትና በልማት ግንኙነታቸውን ማጠናከር መቻሉን ተናግረዋል። የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በማጎልበት በአጎራባች ዞኖችና ወረዳዎች ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ዳብሮ በልማታዊ ስራዎች መደጋገፋቸው ተጠናክሯልም ብለዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ በበኩላቸው የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አብሮነትን በማጠናከር ለትብብር የጎላ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። የጋራ ትርክቶችን በማሰረፅ ረገድም በዓሉ ሚናው ከፍተኛ ነው ብለዋል። እጅ ለእጅ ተያይዘን በአንድነት መጓዝ እንደምንችልና የተጋመደውን ወንድማማችነት እና እህትማማችነት በስራና አብሮ በመልማት ማጠናከር ይገባናል ሲሉም ተናግረዋል።      
በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 17, 2025 58
ድሬዳዋ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ከሪማ አሊ ተናገሩ። የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች እና አመራሮች 20ኛውን የብሔሮች -ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በፓናል ውይይት አክብረዋል። በመድረኩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈጉባ ከሪማ አሊ፤ የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ስናከብር በየአካባቢው ያልተገለጡ እሴቶችን በማስተዋወቅና በመጋራት እንዲሁም ለሀገር ልማትና ብልጽግና በጋራ በመትጋት መሆን አለበት ብለዋል። ዘንድሮም ለልማት በመትጋትና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት ማክበር እንዳለበት አንስተዋል።   በመሆኑም የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫና የፍቅር ምልክት በሆነችው ድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት።   የድሬዳዋ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ሐይር ሐጂ ኑር፤ የበዓሉ መከበር ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት የተጀመሩ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማሳካት በጋራ ለመትጋት መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸው ለውጤታማነት ቅንና ፍትሃዊ አገልጋይ በመሆን መስራት አለብን ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችም በቅንነትና በታማኝነት ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ለለውጥና ማንሰራራት እንሰራለን ነው ያሉት።
 የፖሊስ ተቋምን በማዘመን የሰላምና ልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ይሰራል
Nov 17, 2025 63
ሆሳዕና፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖሊስ ተቋምን ከወቅቱ ጋር በማዘመን የሰላምና ልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ይሰራል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ። በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን "ከጂኦስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሀሳብ ለፖሊስ አመራሮችና አባላት ያዘጋጀው ስልጠና በሆሳዕና ከተማ እየተሰጠ ነው፡፡   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት፤ ፖሊስ ጸጥታና ደህንነትን በማስጠበቅ የክልሉ ሰላምና ልማት እንዲጠናከር አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ፖሊስ ከማህበረሰቡ ጋር የቅርብ ቁርኝት ያለው መሆኑን አስታውሰው ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባና በየአካባቢው ልማት እንዲፋጠን ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።   የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በማፋጠን የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰላምና ደህንነት አጠናክሮ ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ፖሊስ ይህን ሀላፊነቱን በላቅ ብቃት እንዲወጣ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። ለዚህም አሰራሩን ወቅቱን በሚመጥን መልኩ የማዘመን ሥራ እንደሚሰራና የፖሊስ አባላትን አቅም በተለያየ መንገድ የመገንባት ሥራም ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል።
በዓሉ ብዝሃነትን ለማስረጽ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Nov 17, 2025 89
አሶሳ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ብዝሃነትን ለማስረጽ እና አንድነትን ለማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አስካለች አልቦሮ ገለጹ፡፡ አፈ ጉባኤዋ በሰጡት መግለጫ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር አስታውቀዋል። በዓሉ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በስፖርታዊ ውድድሮች፣ በጥያቄና መልስ እንዲሁም ብዝሃነትን በሚያንፀባርቁ ሁነቶች እንደሚከበር ጠቁመዋል። በዓሉ በክልሉ ደረጃ በካማሽ ዞን ካማሽ ከተማ እንደሚከበር የገለፁት አፈ ጉባኤዋ፤ በበዓሉ ላይ ከክልሉ በተጨማሪ የአጎራባች ክልሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ ብለዋል። የካማሽ ዞን ከነበረበት የፀጥታ ችግር ተላቆ በተለያዩ የልማት ስራዎች አመርቂ ውጤቶችን እያሳየ በመሆኑ በዓሉ የዞኑን አሁናዊ ሁኔታ ለሌሎች አካባቢዎች ለማሳየት እንደሚያግዝ ተናግረዋል። የካማሽ ዞን በዓሉን ለማስተናገድ እና እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት መጀመሩንም አፈ ጉባኤዋ ገልጸዋል። የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል በህዝቦች መካከል ያለውን አብሮነት በማጠናከርና ሀገራዊ ትርክት ለመገንባት የሚያግዝ መሆኑን አስታውቀዋል።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የእጩ ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል
Nov 17, 2025 88
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የእጩ ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የግል ዕጩዎች ምዝገባ የሚጀመርበት ጊዜ በቀጣይ ይፋ እንደሚሆንም ጠቁሟል። ምርጫ ቦርድ በጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ባደረገው ጥሪ እጩዎቻቸውን ቦርዱ በገለጸው ሲስተም ተጠቅመው እንደሚያስመዘግቡ ጥሪ አቅርቧል። ምዝገባውን ለማከናወን የሚያስችሉ አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ከህዳር 8 እስከ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በቦርዱ ዋና መሥሪያ ቤት እና ከዚህ ቀደም ፓርቲው ለቦርዱ ባሳወቀው/ባሳወቃት ወኪል አማካኝነት በአካል በመገኘት ሠነዱን እንዲያቀርቡ አሳስቧል። ፖለቲካ ፓርቲዎቹ ቅጾቹን ከ https://nebe.org.et/en/node/725 ላይ ማግኘት እንደሚችሉም ጠቁሟል። በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ለውድድር የተጠቀሙባቸው መወዳደሪያ ምልክቶችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጠቀም ቀዳሚ መብት እንዳላቸው ቦርዱ ገልጿል። ፖለቲካ ፓርቲዎች የሕጉን መሥፈርት የተከተለ የራሳቸውን የመወዳደሪያ ምልክት ማቅረብ እንደሚችሉና በአማራጭነት ቦርዱ ጋር በአካል በመቅረብ ቦርዱ ከሚያቀርበው የመወዳደሪያ ምልክት ዝርዝር ውስጥ መምረጥ እንደሚችሉም አመልክቷል። የግል ዕጩዎች ምዝገባ ቦርዱ በገለጸው መተግበሪያ እንደሚያከናውንና የሚጀመርበትን ጊዜ በተመለከተ ቦርዱ በቀጣይ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የልማት ስራዎች ከዳር እንዲደርሱ የፖሊስ አባላት ሚና ሊጠናከር ይገባል
Nov 17, 2025 54
ቦንጋ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-የተወጠኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶችና ሌሎች የልማት ስራዎች ከግብ እንዲደርሱ የፖሊስ አባላት ያለባቸውን ኃላፊነትና ሚና ሊያጠናክሩ ይገባል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አሳሰቡ። "ከጂኦ ስትራቴጂካዊ ኩስመና ወይ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሃሳብ ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ የፖሊስ አመራሮችና አባላት የተዘጋጀ ስልጠና በቦንጋ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።   የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ እንደገለፁት፣ ከለውጡ ወዲህ በርካታ ፈተናዎች ውስጥ በማለፍ በርካታ ድሎችን ማስመዝገብ ተችሏል። ለውጡ ብዙ መስዋእትነት የተከፈለበት መሆኑን ጠቅሰው የፖሊስ አባላቱ ከዚህ ቀደም ከነበረው የበለጠ ትጋትና ቁርጠኝነት እንዲሁም ጀግንነት የሚጠይቁ ተግባራት ከፊታቸው እንዳሉ ሊገነዘቡ እንደሚገባም አንስተዋል። ስለሆነም በመንግስት የተወጠኑ የልማት ስራዎች ከዳር እንዲደርሱ የፖሊስ አባላት ኃላፊነትና ሚና ሊጠናከር ይገባል ብለዋል። የፖሊስ አባሉ አሁን ያለውን ክልላዊ፣ ሀገር አቀፋዊና ቀጠናዊ ሁኔታዎችን በተገቢው ለማወቅና ለመረዳት የሚያስችለው ስልጠና መሆኑን አፈ-ጉባኤው አስረድተዋል። የክልሉ ሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ዓለሙ፤ ስልጠናው የዓለም-አቀፉን የጂኦ ፖለቲካ ሁኔታ በመገንዘብ ተገቢውን ቁመና ለመያዝና የፖሊስ ሠራዊቱን አረዳድ የተሻለ ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።   ስልጠናው ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥም ታውቋል።
የክልሉ ፖሊስ ሕግን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ ነው
Nov 17, 2025 84
አሶሳ፤ ሕዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት እያስጠበቀ የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ "ከጂኦስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሐሳብ ለክልሉ ፖሊስ እና ፀጥታ አካላት የሚሰጠውን ስልጠና አስጀምረዋል።   በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን እንደተናገሩት፤ የፀጥታ አካላት ዋነኛው ተልዕኮ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅና ሕግ ማስከበር ነው። ተለዋዋጭ የሆነውን ወቅታዊ ጂኦፖለቲክስ በመረዳት እና በተደመረ አቅም የክልሉን ሰላም ለመጠበቅ የሚያግዝ የፀጥታ ሀይል እንዲኖር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።   ከዚህ ባለፈ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ሀገሪቷ የምታከናውናቸው ግዙፍ የልማት እንቅስቃሴዎች ደህንነት ማስጠበቅ እንዳለባቸውም አሳስበዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ሀሩን ዑመር በበኩላቸው፤ ስልጠናው በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የፖሊስ አባላት ተቀራራቢ ግንዛቤ እንዲኖራቸው እና ለላቀ ተልዕኮ ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።   ለሁለት ቀናት በተሰናዳው ስልጠና ላይ የክልሉ የፖሊስ አመራሮች እና አባላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ማህበራዊ
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት እየሰጠ ያለውን አገልግሎት ማጠናከር ይገባል
Nov 17, 2025 33
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት እየሰጠ ያለውን አገልግሎት አጠናክሮ መቀጣል እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎትን የ2018 ዓ.ም የአንደኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ገምግሟል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ባቀረቡት ሪፖርት እንዳሉት፤ በመጀመሪያው ሩብ አመት 545 ሺ 491 ፓስፖርት ለዜጎች ተደራሽ ተደርጓል። የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት (ኢ-ፓስፖርት) ደግሞ 14 ሺህ 818 ለሚሆኑ አገልግሎት ፈላጊዎች ተደራሽ ተደርጓል ብለዋል። ከገቢ አኳያም በሩብ ዓመቱ 11 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ፤ በዚህም ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ማሰባሰብ መቻሉን አስረድተዋል። ሀሰተኛ ፓስፖርት ይዘው የተገኙ የአገር ውስጥና የውጪ ዜጎች በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉንም አብራርተዋል። በሩብ ዓመቱ 860 ሀሰተኛ ሰነድ ይዘው ፖስፖርት ለመውሰድ የሞከሩ የውጭ እና የአገር ውስጥ ዜጎች በቁጥጥር ስር ውለው በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉንም ገልጸዋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሯ ሰላማዊት ገለጻ፤ በሩብ ዓመቱ በድንበር አካባቢ በተከናወነ የቁጥጥር ሥራ 16 ሺህ 465 የሚሆኑ የውጭና የሀገር ውስጥ ዜጎች በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡና ከኢትዮጵያ ሊወጡ ሲሉ ተይዘዋል። በተቋሙ ሪፎርም ከተደረገ ወዲህ ከተገልጋዮች የሚነሱትን ጥያቄዎች በሟሟላት በመደበኛ በስድስት ወር ይሰጥ የነበረውን ፓስፖርት በሁለት ወራት እየተሰጠ መሆኑን አብራርተዋል። ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበርም ሕገ-ወጥነትን በመከላከል ዙሪያም የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ በበኩላቸው፤ አገልግሎቱ የዲጂታል አሰራር ሥርዓትን በመከተል መስጠት የጀመረውን አገልግሎት ይበልጥ ሊያጠናክር ይገባል። ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማቅረብ፣ ቅርንጫፎቹን ማስፋፋት እንዲሁም ተቋማዊ ደህንነት ለማጠናከር የጀመራቸውን ተግባራት ይበልጥ ማጠናክር እንደሚኖሩበትም አስገንዝበዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) በማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት፤ አገልግሎቱ ሕግን በማስከበር ላይ ውጤታማ ሥራ በማከናወኑ የሚበረታታ እና በጠንካራ ጎን የሚጠቀስ ነው። ሕገ-ወጥነትን መከላከል ላይ የጀመራቸውን ሥራዎች ማጠናከር እንዲሁም የድንበር አካባቢ ቁጥጥር ሥራዎችን በትኩረት መከወን እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በአዲስ አበባ ይካሄዳል 
Nov 17, 2025 36
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡- የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል ይደረጋል። የሽልማት ስነ ስርዓት “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶ ግራፈር፣ ሀገር በቀል/ ብሄራዊ ቋንቋ ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ከእ.አ.አ 2023 ጀምሮ እየተካሄደ የሚገኝ ዓመታዊ ሁነት ነው። የ2023 ሽልማት በጅቡቲ፣ የ2024ቱ በኬንያ ናይሮቢ መካሄዱ ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የደረሰችበትን እድገት የሚየሳዩ እና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች እየተገነቡ ነው - ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ
Nov 17, 2025 35
ባህር ዳር፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የደረሰችበትን እድገት የሚያሳዩ እና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች እየተገነቡ መሆኑን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ አስታወቁ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና ማሕበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የባሕር ዳር ስታዲየምንና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩትን ተመልክተዋል።   የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በሀገሪቱ የስፖርት ልማት፣ ውጤታማነትን በሚያረጋግጥ አግባብ እየተከናወነ ነው። ከለውጡ ወዲህ ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች አንዱ የስፖርት ልማት መሆኑን ጠቅሰው፤ ለዚህም ጥናት ላይ የተመሰረተ ስትራቴጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ ይገኛል ብለዋል። በተለይም ህፃናትና ታዳጊዎች ላይ በመመስረት ተተኪና ብቃት ያላቸው ስፖርተኞችን በሁሉም ዘርፎች ማፍራት የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳዎችን ችግር በመፍታት ውጤታማ ስራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በመላ ሀገሪቱ በርካታ መካከለኛና አነስተኛ ስታዲየሞች መገንባት ተችሏል ብለዋል።   እንዲሁም ነባርና አዳዲስ ታላላቅ ስታዲየሞች ግንባታ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን በጠበቀ አግባብ እየተገነቡ መሆኑን ጠቁመው መንግስት ዘርፉን ለማሳደግ ልዩ ትኩረት በመስጠት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሰስ እያደረገ ይገኛል ነው ያሉት። የባህር ዳር፣ ድሬዳዋ፣ አርባ ምንጭ፣ አደይ አበባ እና ሌሎች ታላላቅ ስታዲየሞች የፊፋንና ካፍን ደረጃ በጠበቀ መንገድ እየተገነቡ መሆኑን ጠቅሰው ከፍተኛ ክትትል እየተደረገባቸው በሙያ ታግዘው እየተሰሩ ነው ብለዋል። አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በቀጣይ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ስሟ ከፍ ብሎ እንዲጠራ የሚያስችሉ ብቃት ያላቸው ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል። መንግስት ለስፖርት ልማት ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱንና እየተገነቡ ያሉ ስታዲየሞች የኢትዮጵያን ገፅታና እድገት በሚያሳይ አግባብና ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።   በኢትዮጵያ የስፖርት ልማት ዘርፍ የህዝብ ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጥ መንገድ እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና ማሕበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ(ዶ/ር ) ናቸው። ስፖርት ለኢኮኖሚ እድገት ካለው ፋይዳ ባሻገር ማህበረሰቡ በትርፍ ጊዜው መዝናናት እንዲችል ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ ይገኛል ብለዋል። የባህር ዳር ስታዲየም ግንባታ ዓለም አቀፍ መስፈርት ባሟላ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን ማረጋገጥ እንደተቻለ ጠቅሰው፤ በቀጣይ የስታዲየሙ ጥላ በትብብር የሚሰራበትን ሁኔታ ስራ አስፈፃሚው ሊያመቻች ይገባል ነው ያሉት። አሁን ላይ ስፖርት ጨዋታ ብቻ አይደለም ያሉት ምክትል ሰብሳቢው ስፖርት የሀገር ሉዓላዊነት፣ ዲፕሎማሲ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ መስተጋብርና ሌሎች ሁሉን አቀፍ ጉዳዮችን የያዘ መሆኑንም ገልጸዋል። በዘርፉ እየተከናወኑ የሚገኙ ልማቶች የበለጠ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውና ለዚህም ምክር ቤቱ ተገቢውን እገዛና ክትትል እንደሚያደርግ ተናግረዋል።   የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሕዝብ ግንኙነት አማካሪ እርዚቅ ኢሣ በበኩላቸው፤ የባሕር ዳር ስታዲየም የካፍና ፊፋ መስፈርቶችን መሰረት በማድረግ እየተገነባ መሆኑን ጠቁመው ትላልቅ ጨዋታዎችን ማስተናገድ እንዲችል ሆኖ በጥራት እየተሰራ ነው ብለዋል። ለስታዲየሙ የሚያስፈልገው የመጠለያ ስራም በቀጣይ የክልሉና የፌደራል መንግስት በትብብር እንደሚሰሩበት ተናግረዋል።
የጸጥታ ሀይሉ የክልሉን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ወቅቱ በደረሰበት ክህሎትና እውቀት ራሱን ማሳደግ ይገባዋል     
Nov 17, 2025 47
ቦንጋ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የጸጥታ ሀይሉ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ወቅቱ በደረሰበት ደረጃ እውቀትና ክህሎቱን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ገለፀ። “ከጂኦስትራቴጂካዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና” በሚል መሪ ሀሳብ የክልሉን የፀጥታ ሀይል ሙያዊ እውቀትና ክህሎት የሚያሳድግ የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሀብታሙ አለሙ በወቅቱ እንዳሉት፤ የጸጥታ ኃይሉ የክልሉን ጸጥታና ልማት ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ሚና እየተወጣ ይገኛል። ይህን ታላቅ ኃላፊነት ለመወጣትም የጸጥታ አካላቱን እውቀትና ክህሎት ወቅቱ በደረሰበት ደረጃ ይበልጥ በማሳደግ ለህዝቡ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችልበትን አቅም ማሳደግ ላይ መስራቱን አንስተዋል። ተልዕኳችን ጥልቅ ራዕያችን ሰፊ ነው ያሉት ምክትል ቢሮ ሀላፊው የፖሊስ አመራሩንና አባሉን አቅም በመገንባት በህዝብ ዘንድ የሚከበርና የሚታመን የፖሊስ ተቋም ለመገንባት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። የክልሉ ፖሊስ መዋቅር በርካታ ሪፎርሞችን በማከናወን የተሻለ ልምድና አቅም ያለው ሰራዊት መገንባት መቻሉንና በቀጣይም ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።   በክልሉ የተመዘገቡ ለውጦችን ለማስቀጠል የጸጥታ ኃይሉን ማጠናከር ላይ መስራት አስገዳጅ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወንድሙ ኩርታ ናቸው። ከዚህ የተሻለ ለውጥ ለማምጣትና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የላቀ ቁርጠኝነትና የዓላማ ፅናት ያነገበ የፖሊስ አባል ያስፈልጋል ብለዋል።   የፌደራል ፖሊስ የህግና ሰብዓዊ መብት ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ፋሲል አሻግሬ ስልጠናው ሀገራዊ፣ አህጉራዊና አለም አቀፋዊ አካባቢያዊ ሁኔታዎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በስራ ላይ ያሉ እንቅፋቶችን በመፍታት ህዝብን የበለጠ ለማገልገል እንደሚያግዝ አብራርተዋል። ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው ስልጠና ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የፖሊስ አመራሮችና አባላት እየተሳተፉ ነው።
ኢኮኖሚ
የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና በነባሮቹ ላይ እሴት በመጨመር የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Nov 17, 2025 47
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የቱሪዝም ሚኒስቴር አዳዲስ መዳረሻዎችን በማልማትና ነባሮቹ ላይ እሴት በመጨመር ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራትን እንዲያጠናክር የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳሰበ። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቱሪዝም ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማትን የ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ገምግሟል። ኢትዮጵያ ያላትን ባህላዊና ተፈጥሯዊ የቱሪዝም ሃብቶች ከማልማት ባሻገር በስፋት ለማስተዋወቅ የተጀመሩ ሥራዎች የኢትዮጵያን ምድረ-ቀደምትነት የሚያረጋግጡና የአገርን ገጽታ የሚገነቡ ስለ መሆናቸው ተነስቷል። መንግስት ዘርፉን ከአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ማድረጉ በራሱ ለዘርፉ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱም ተገልጿል፡፡ በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመሩ የገበታ ለአገር፣ ገበታ ለትውልድና ገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች ለዘርፉ መነቃቃት ከፍተኛ ሚና መጫወታቸው ተነግሯል። የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለሚኒስቴሩ ካነሳቸው ጥያቄዎች መካከል የገበታ ፕሮጀክቶችን ከማስተዋወቅ ባለፈ ሚኒስቴሩ በራሱ አቅም አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማት ያከናወናቸው ተግባራት ይጠቀሳሉ። የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ እና የሥራ ባልደረቦቻቸው በቋሚ ኮሚቴው ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ጊዜ ተቋማቸው በሩብ ዓመቱ አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማልማት ተመራጭና ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ የተለያዩ ተግባራትን ማከናወኑን አብራርተዋል። ከእነዚህ ውስጥ የጅማ አባጅፋር ቤተ-መንግስት ጥገናና ዕድሳት፣ የባሌ ብሄራዊ ፓርክ መዳረሻ ልማትና ፕሮጀክት፣ የጂኦ ፓርኮች ልየታና ልማት ስራን ለአብነት አንስተዋል። በነባር መዳረሻዎች ላይ እሴት በመጨመር ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ በፋሲል አብያተ መንግስታት ''ሕይወት በቤተ መንግስት'' የተሰኘ ትዕይንት መዘጋጀቱን አንስተዋል። በዚህም በዓብያተ መንግስታቱ ሲከወኑ የነበሩ የአስተዳደርና የፍትህ፣ የግብር ማብላት ስርዓቶችን ጨምሮ የኪነ-ጥበብና የዕደ-ጥበብ ሥራዎች እሴቶቻቸው ተጠብቀው እንዲቀርቡ ተደርጓል ብለዋል። ጥንታዊውን የደጋ እስጢፋኖስ ገዳም ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ይዞታውን ጠብቆ ለጎብኚዎች ተደራሽ መደረጉንም ገልጸዋል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ ከባቡር ትራንስፖርት ጋር ያላትን ቁርኝት በሚያሳይ መልኩ የቱሪስት መስህብ ለማድረግ የተሰሩ ሥራዎችን ለአብነት አንስተዋል። በተያዘው ዓመት የቱሪዝም ሃብቶችን ለይቶና ደረጃ አውጥቶ የመዳረሻ ልማት ለማከናወን ከክልሎች ጋር በጋራ እየሰራን ነው ብለዋል። በተጨማሪ ቱሪዝም በአጠቃላይ የአገር ወስጥ ምርት ያለው ድርሻ ምን ያህል እንደሆነ ቋሚ ኮሚቴው ማብራሪያ ጠይቋል። ሚኒስትሯ ዘርፉ ለአጠቃላይ አገራዊ ምርት ዕድገት ያለውን ሚና በአግባቡ ለመለየት ባለፈው ዓመት የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አሻ ያህያ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በተለየም የአገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ቁጥር ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት በጥንካሬ የሚወሰዱ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ የበርካታ ባህላዊና ተፈጥሯዊ የቱሪዝም ሃብት ባለቤት እንደመሆኗ ይህን ሃብት ገልጦ የማሳየት፣ የመጠቀምና የማስተዋወቅ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል። ሚኒስቴሩ በቱሪስት መዳረሻ ልማትና እሴት መጨመር ላይ የጀመራቸውን ተግባራት የበለጠ እንዲያጠናክርም አሳስበዋል። ሚኒስቴሩ ከአገልግሎት አሰጣጥ፣ ከቅርስና የዱር እንሰሳት ጥበቃ ጋር በተያያዘ የሚታዩ ክፍተቶችን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት መፍታት አለበት ሲል ቋሚ ኮሚቴው አሳስቧል።
በክልሉ በየአካባቢው የሚገኙ ፀጋዎችን በመለየትና በማልማት ለስራ ፈጣራ ለማዋል ትኩረት ተሰጥቷል
Nov 17, 2025 49
ባሕር ዳር፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በየአካባቢው የሚገኙ ፀጋዎችን በመለየትና በማልማት ለስራ ፈጣራ የሚያውል ታታሪ ትውልድ ለመገንባት ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ። በክልሉ በበጀት ዓመቱ አራት ወራት ከ260ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው የክልሉ ስራና ክሕሎት ቢሮ አስታውቋል። ቢሮው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በጋራ እንገነባለን በሚል መሪ ሃሳብ ዓለም አቀፍ የስራ ዕድል ፈጠራ ሳምንት የመክፈቻ መርሃ ግብር ዛሬ አካሂዷል።   የቢሮ ኃላፊው ስቡህ ገበያው(ዶ/ር)፤ የዓለም አቀፍ የሥራ ፈጠራ ሳምንትን ስናከብር በየአካባቢው የሚገኙ ፀጋዎችን በመለየትና በማልማት ለስራ ፈጣራ የሚያውል ታታሪ ትውልድ ለመገንባት በማለም ነው ብለዋል። ቢሮው የክልሉን ፀጋ በመለየትትና በማልማት ለስራ ፈጠራ ለማዋል ሲሰራ መቆየቱን አውስተው፤ በሂደቱም ስራ ፈላጊዎችን በመመዝገብና ፍላጎታቸውን መሰረት በማድረግ አሰልጥኖ ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ገልጸዋል። የዛሬው መርሃ ግብርም በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመፍታት የተጀመሩ የስራ ፈጠራ ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል መሆኑን አስረድተዋል። በበጀት ዓመቱ ከተያዘው አቅድ ውስጥ ባለፉት አራት ወራት ለ265ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉን የገለጹት ደግሞ የቢሮው ምክትል ኃላፊ አወቀ ዘመነ ናቸው። የስራ ዕድሉ የተፈጠረው በኮንስትራክሽን፣ በከተማ ግብርና፣ በዕደ ጥበብ፣ በብረትና እንጨት ስራና ሌሎች ዘርፎች መሆኑን ጠቅሰዋል። ለስራ ዕድል ተጠቃሚዎችም ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ በመደበኛና በተዘዋዋሪ ብድር፣ ከ4ሺ 300 ሄክታር በላይ መሬትና 719 ሼዶች ተገንብተው መተላለፉን አስታውቀዋል። አፈጻጸሙ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ መሆኑን ገልጸው፤ ለዚህም የተካሄደው ቅንጅታዊ አሰራር ያስገኘው ውጤት ነው ብለዋል። በኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት የአማራ ክልል ፕሮግራም አስተባባሪ ይበልጣል ኤልያስ በበኩላቸው፤ በአማራ ክልል የስራ ፈላጊዎችን እውቀትና ክህሎት ለማሳደግ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። ስልጠናው ከክልል እስከ ወረዳ ከሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር በመቀናጀት እየተከናወነ መሆኑን አረጋግጠዋል። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የቢሮው አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በባሌ ዞን ወደ ኢንቨስትመንት ለተሸጋገሩ 112 አርሶ አደሮች እና ማህበራት የኢንቨስትመንት ፍቃድ ተሰጠ
Nov 17, 2025 47
ሮቤ፤ ህዳር 8/2018 (ኢዜአ)፦ በባሌ ዞን ወደ ኢንቨስትመንት ለተሸጋገሩ 112 አርሶ አደሮች እና ማህበራት የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን የዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ገለጸ። የተደረገላቸው የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ለተሻለ ሥራ እንደሚያነሳሳቸው ወደ ኢንቨስትመንት ተሸጋገሩት አርሶ አደሮች ገልጸዋል። የዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ኢብሮ እንዳሉት በዞኑ ወደ ኢንቨስትመንት በመሸጋገር እውቅና ያገኙት 112 አርሶ አደሮች እንዲሁም ኢንተርፕራይዞች ናቸው። ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮችና ኢንተርፕራይዞች ባለፉት ዓመታት በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ ከመሆን ባሻገር ከ422 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል። ኢንቨስተሮቹ ወደ ስራ ሲገቡ 5 ሺህ 600 ለሚጠጉ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል እንደሚፈጥሩም አክለዋል። በዞኑ አርሶ አደሩ በመደበኛነት ከሚያመርተው ሰብል በተጓዳኝ የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ተግባራዊ በማድረግ ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት የሚሸጋገሩ አርሶ አደሮች ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል። ወደ ኢንቨስትመንት ለተሸጋገሩት አርሶ አደሮችና ማህበራት በሚሰማሩበት የስራ መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ የመሬት አቅርቦትና ሌሎች የተለያዩ ማበረታቻዎች እንደሚደረግላቸውም አመልክተዋል። ባለፉት ዓመታት በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ በመሆን ወደ ኢንቨስትመንት ከተሸጋገሩ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ኮርሳ አሰፋ፤ በግብርና በመሰማራት በሚያመርቱት ስንዴና ሌሎች ሰብሎች ልማት 9 ሚሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ወደ ኢንቨስትመንት በመሸጋገራቸው 10 ሄክታር መሬት በኢንቨስትመንት ማበረታቻነት ማግኘታቸውን ገልፀዋል። በአካባቢው ከሚመረተው የስንዴ ምርት በተጨማሪ ገበያ ተኮር የሆኑ ቅመማ ቅመም በማምረት በሚያገኙት ገቢ 10 ሚሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን የተናገሩት ደግሞ ሌላው አርሶ አደር ሐጂ ኢብራሂም ከድር ናቸው። በአሁኑ ወቅት በኢንቨስትመንት ማበረታቻነት የተሰጣቸው መሬትና የእውቅና ሰርተፊኬት ለተሻለ ሥራ እንዳነሳሳቸውም አክለዋል። አቶ ግርማ ከተማ በበኩላቸው በጥቃቅንና አነስተኛ ንግድ ውጤታማ በመሆን ባስመዘገቡት 2 ሚሊዮን ብር ካፒታል ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን ተናግረዋል። በዞኑ የዛሬዎቹን ሳይጨምር 200 የሚሆኑ ግንባር ቀደም አርሶ አደሮች ባስመዘገቡት ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ካፒታል ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸው ተገልጿል።
ጣልያን በኢትዮጵያ ያላትን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራች ነው
Nov 17, 2025 69
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-ጣልያን የቤቶች ልማትን ጨምሮ በኢትዮጵያ ያላትን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራች እንደምትገኝ በኢትዮጵያ የጣልያን ኤምባሲ የንግድ ኮሚሽነር ክላውዲዮ ፓስኩዋሉቺ ገለጹ። ኮሚሽነር ክላውዲዮ ፓስኩዋሉቺ ጣልያን እና ኢትዮጵያ ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነት ቢኖራቸውም የንግድ ትብብራቸው የሚፈለገውን ያህል እንዳላደገ ለኢዜአ ገልጸዋል። ጣልያን ወደ ኢትዮጵያ የምትልካቸውን ምርቶች እንዲሁም ቡና እና ማዕድናትን ጨምሮ ከኢትዮጵያ የምታስገባቸውን ስትራቴጂካዊ ምርቶች ለማሳደግ እቅድ መያዟን አመልክተዋል። ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የንግድ ግንኙነት ለማጎልበት እየተከናወነ ያለው ስራ በጥሩ መንገድ ላይ ይገኛል ብለዋል። ኢትዮጵያ በጣልያን ግዙፍ የኢንቨስትመንት እቅድ ቅድሚያ ከተሰጣቸው ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን ነው የገለጹት ኮሚሽነሩ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ለማልማት እና የጣልያንም ኩባንያዎች በግላቸው እና ከኢትዮጵያ ኩባንያዎች በሽርክና መስራት የሚችሉባቸውን እድሎች ለመፍጠር እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ማህበረሰብ ተኮር የቤት ግንባታን ጨምሮ ሌሎች ኢኒሼቲቮች ላይ ውይይቶች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፥ ይህም በኢንቨስትመንት ሽርክና ለመስራት ያለውን እድል የሚያመላክት እንደሆነ ገልጸዋል። የሁለቱን ሀገራት የንግድ ግንኙነት ለማሳደግ የሚያስችሉ እድሎች ከፊታችን አሉ ያሉት ኮሚሽነሩ አቅምን ወደ ሚታይ ውጤት ለመቀየር በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመስጠት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል
Nov 17, 2025 91
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የመንግስት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመስጠት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመርያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡ ሚኒስቴሩ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ፣ በዲጂታል መታወቂያና በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና አበረታች ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት ከተቋማት ጋር በመቀናጀት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ስራዎች በማከናወን ላይ ነው።   ቋሚ ኮሚቴው ሚኒስቴሩ በቴክኖሎጂ የተደገፉ የመንግስትና የንግድ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል አስቻይ ሁኔታ በመፍጠር ሀገራዊ ኢ-ኮሜርስና የኢንተርኔት የንግድ ግብይት ስርዓትን ለማሳደግ ምን እየሰራ እንደሆነ ጥያቄ አቅርቧል። የኢትዮ-ኮደርስ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ስልጠና ለመስጠት የሚኒስቴሩ ድጋፍና ክትትል ምን ይመስላል በሚለው ላይም ማብራሪያ ጠይቋል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) የተቋማቸውን አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት እንዳስታወቁት፤ ባለፉት ሶስት ወራት በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል፡፡ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ከተቋማት ጋር በመቀናጀት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ስራዎች መከናወናቸውን በመግለጽ። በዚህም 10 የንግድ ተቋማት ወደ ኤሌክትሮኒክ ግብይት መግባታቸውን፣ ሶስት የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማሳለጫ ፕላት ፎርሞችን በማዘጋጀት ለ56 አይሲቲና ዲጂታል ኢንዱስትሪዎች ብቃት ማረጋገጫ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።   በሌላ በኩል በኦንላይን የሚሰጡ የመንግስት አገልግሎቶችን በሚመለከት የተያዘውን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ማሳካት መቻሉንም አስታውቀዋል። ከዲጂታል መታወቂያ ጋር በተያያዘ በ2018 የመጀመርያ ሩብ ዓመት አምስት ሚሊዮን ተጠቃሚዎች አገልግሎቱን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል። በኢትዮ-ኮደርስ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ስልጠና ባለፉት ሶስት ወራት ከ ሁለት ነጥብ አራት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው ሚኒስትር ዴኤታው ያነሱት። ከተሞችን በዲጂታል አድራሻ ስርዓት ለማካተት በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰው፤ በሩብ ዓመቱ የአምስት ከተሞች ትግበራን የማጠናቀቅ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። ሀገራዊ ኢኖቬሽን ምርምርና ቴክኖሎጂን በሚመለከት በሩብ ዓመቱ ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ነው ያስታወቁት፡፡   እንዲሁም 205 ችግር ፈቺ ምርምሮችን በምርምር እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማከናወን መቻሉንም አንስተዋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፤ ሚኒስቴሩ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ የተቋማትንና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል። የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አበረታች መሆኑን ጠቅሰው፤ ተቋማት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት እንዲሰጡ በቅንጅት መስራት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ኢንዱስትሪ ለመሸጋገር በምታደርገው ጉዞ ቴክኖሎጂ አስፈላጊ በመሆኑ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር የሚደረገው ቅንጅታዊ አሰራር ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት። ተቋማት ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለመጠቀም ዝግጁ እንዲሆኑ ማገዝ እንደሚገባ አሳስበው፤ ቴክኖሎጂውን አስመልክቶ ለተቋማትና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶር) በመጨረሻም በቋሚ ኮሚቴው የተነሱ ክፍተቶችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በትኩረት እንሰራለን ሲሉ አረጋግጠዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች ተተግብረዋል - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
Nov 17, 2025 71
አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች መተግበራቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጠባቂነትን አስወግዶ በሀሳብ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል ያሳየ ተቋም መሆኑንም ጠቅሰዋል። የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴርና ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ተከፍቷል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር)፣ ዲፕሎማቶችና ሌሎች ተሳታፊዎች በመክፈቻ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተዋል። ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ስሟን ከፍ ያደረጉ አንቱ የተባሉ ምስጉን፣ ታታሪ ኢንተርፕርነሮችስ ስትፈጥር ቆይታለች።   ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስቷ መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትን የገነባችው፣ ሕጎችን ያወጣችው ባለፉት ሰባት ዓመታት ነው ብለዋል። በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት የኢንተርፕርነርሽፕ ሥነ ምህዳርን ተቋማዊ ማድረግ የሚያስችል እንቅስቃሴ መደረጉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የሀሳብ ብዝሃነት ጸጋ ለሀሳብ ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጠባቂነትን አስወግዶ በሀሳብ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል በተግባር አሳይቷል ነው ያሉት። በዚህም ባለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች ተተግብረዋል ብለዋል። ኢትዮጵያ የኢንተርፕርነሮች መፍለቂያ ትሆናለች ያሉት ሚኒስትሯ፤ መንግሥት የኢንተርፕርነርሽፕ ምህዳሩን ምቹ ማድረጉን ገልጸዋል። ሀሳብ ካለ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል አምናለሁ ያሉት ሚኒስትሯ፤ ይህን ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል እምቅ ሀገራዊ አቅም፣ ፖሊሲና ተቋም ተገንብቷልም ብለዋል። የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያ ኢንተርፕርነር መሆንና እንዴት እንደምትሆን በግልጽ አስቀምጧል ነው ያሉት።   የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሽፕ ሁነቶችን በማዘጋጀት ብራዚልን በመቅደም ከዓለም አንደኛ ሆናለች ብለዋል። ኢንተርፕርነሮች የፈጠራ መፍትሔዎችን ወደ መሬት የሚቀይሩ፣ ምኞትን የሚያሳኩ፣ አይቻልምን ችለው የሚያሳዩ ፈር ቀዳጅ ባለራዕዮችና ከዋኞች ናቸው ነው ያሉት። ኢንተርፕርነሮች ሀገር ሰሪዎች መሆናቸውን ጠቁመውም በዘንድሮው 12ኛው የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ስልጠናዎች፣ የፈጠራ ሀሳብ ውድድሮችና ጥናቶች ይከናወናሉ ብለዋል። በኢትዮጵያ የሚወሰን ሳይሆን ድንበር ተሻጋሪ ሥራ ጀምረናል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የመጨረሻ ግባችን አይበገሬ ማህበረሰብ፣ ዜጋና ሀገር መገንባት ነው ሲሉም ገልጸዋል።
የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 17, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በአፋር ክልል ያለውን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የክልሉን መሶብ (ኮራ) የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሰመራ ሎጊያ ከተማ ስራ አስጀምረዋል። በመርኃ ግብሩ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ (ዶ/ር) እንዲሁም የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።   የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በዚሁ ወቅት፤ ለአገልግሎቱ መጀመር አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበው፤ በቀጣይ በተለያዩ የክልሉ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ለማስፋፋት እንደሚሰራ ተናግረዋል። በክልሉ ያለውን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል፡፡ 10ኛው የከተሞች ፎረም በሰመራ ሎጊያ ከተማ መከናወኑ ለከተማዋ ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑንም ጠቁመዋል። የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለከተሞች ብዙ ትርጉም አለው ብለዋል።   አገልግሎቱ ዜጎች የሚገባቸውን አገልግሎት በተቀላጠፈ ሁኔታ የሚያገኙበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በሰመራ ሎጊያ የተገነባው የመሶብ ማዕከል የሚደነቅ ስራ መሆኑን ጠቁመዋል። ማዕከሉ መልካም አስተዳደርን በማስፈን በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ለውጥ እንደሚያመጣ ተናግረዋል። በተጨማሪም በአንድ ቦታ በርካታ አገልግሎት በመስጠት ለዜጎች እፎይታን የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።   መሶብ የተሳለጠ ሰው ተኮር አገልግሎት የሚሰጥበት ማዕከል መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ሀይሌ(ዶ/ር) ናቸው።   የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚፈታ እንዲሁም የአገልግሎት ልህቀት ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል። ማዕከሉ ዜጎች ከመንግስት የሚፈልጉትን አገልግሎት በተቀላጠፈ ሁኔታ የሚያገኙበት የኢትዮጵያ ማንሰራራት መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል። የአፋር ክልል በዚህ ረገድ ያቋቋመው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚደነቅ ስራ መሆኑን ገልጸው ኮሚሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም ነው 
Nov 17, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት ቀይሮ ወደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ሕንፃ በተዛወረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) መልዕክት አስተላልፈዋል። በዚሁ ወቅትም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአምስት ዓመት ውስጥ አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ መድረሱ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ የሮቦቶችን ሶፍትዌር ብቻ ሳይሆን ውጫዊ የአካል ክፍልን (ሃርድዌር) መሥራት ጀምሯል ብለዋል። ድሮን ማምረት ብቻ ሳይሆን የማነጋገር ዐቅም እየፈጠረ ያለ ተቋም መሆኑንም ተናግረዋል።   አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ደረጃ የሚወዳደር አሠራርን የሚከተል መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ምርቶችን አውጥቷል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የጡት ካንሰር ልየታ ላይ ትልቅ ውጤት ማምጣት መቻሉን እና ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርቲፊሻል ዐዋቂዎች ዘንድ ተቀባይነት ብሎም የባለቤትነት መብት ያገኘ ሥራ ነው ብለዋል። በግብርና ዘርፍም የቡናና የሌሎች አዝርዕቶች በሽታ የሚለይ ፕሮዳክት መመረቱን በመጠቆም ለዚህም ባለቤትነት መብት መኖሩን አስረድተዋል። በሌላ በኩል መሶብ የሚባለውን በአንድ ማዕከል ከ100 በላይ አገልግሎቶች የሚሰጠውን ሲስተም የገነባው አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መሆኑን አስታውቀዋል። ገንዘብ ሚኒስቴር፣ገቢዎች ሚኒስቴር እና ጉምሩክ ኮሚሽንን ጨምሮ ተቋማት አሠራሮቻቸውን ለማዘመን የሚገለገሉባቸው በርካታ ሲስተሞችን መገንባት መቻሉን አንስተዋል። የኢንስቲትዩቱ ሞቶ ኤ አይ ለሁሉም ስለሆነ፤ ከዚህ አንጻር አንዱ ማሳያ ክላውድ ኮምፒቲንግ መሆኑን አንስተዋል።   ለምሳሌ ከዳታ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ትግርኛ እና አፋርኛ የአንዱ ቋንቋ ተናጋሪ ሦስተኛ ሰው ሳያስገባ ከሌላኛው ቋንቋ ተናጋሪ ጋር መግባባት የሚችልበትን መንገድ፣ በጽሑፍ የገባን መልዕክት ወደ ድምጽ የመቀየር፣ በድምጽ ያለ መልዕክትን ወደ ጽሑፍ የመቀየርና መሰል አገልግሎት ለመስጠት በሺህ ሰዓቶች የሚቆጠሩ ኦዲዮዎችን ዳታዎች በማስገባት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። የግብርና ሪቮሉሽን አንድ ሁለት ሦስት እያለ መጥቷል እኛ እዛ ውስጥ አልነበርንም፤ ቴክኖሎጂካል ሪቮሉሽን ነበሩ፣ ኢንደስትሪያል ሪቮሉሽኖች ነበሩ፤ በእነዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በሬና ሰውን ማላቀቅ ሳትችል የኖረችበት ዋናው ምክንያት አዲስ ዕውቀት፣ አዲስ ልምምድ፣ አዲስ ፈጠራ ሲፈጠር ያንን ነገር ለማወቅና ለመከተል የነበረው ጉጉት፣ ዝግጁነት እና እሳቤ አናሳ ስለነበረ ነው ሲሉ ገልጸዋል። እዚህ ላይ ለመተካከል ሳይሆን ጥሩ ተከታይ ለመሆን እንኳ በእጅጉ ይቀረን ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አሁን ሁኔታው መቀየሩን በአጽንኦት አስረድተዋል። ስለዚህ ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮሉሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን ሲሉ አስገንዝበዋል።
ስፖርት
ብቁና ተፎካካሪ ስፖርተኞችን ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Nov 17, 2025 58
ባሕርዳር፤ ሕዳር 8/2018(ኢዜአ)፡- በሁሉም የስፖርት ዓይነቶች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ የሚወክሉ ብቁና ተፎካካሪ ስፖርተኞችን ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ ገለጹ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና ማሕበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የባሕር ዳር ስታዲየምን እየጎበኙ ነው። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ እንደተናገሩት፤ ለስፖርት ዘርፍ እድገት በትኩረት እየተሰራ ነው። ይህም እግር ኳስን ጨምሮ በሁሉም የስፖርት ዓይነቶች ኢትዮጵያን ወክለው በዓለም አቀፍ መድረክ ብቁ ተፎካካሪ ስፖርተኞችን ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። ከእነዚህም ደረጃቸውን ጠብቀው እየተከናወኑ ያሉ ታላላቅ፣ መካከለኛና አነስተኛ ስታድየሞች ግንባታን ጠቅሰዋል።   ይህም ታዳጊና ህፃናትን መሰረት ያደረገ እንደሆነ ጠቁመው፤ ተግባሩ ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና ማሕበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በሀገሪቱ ብቁ ስፖርተኞችን ለማፍራት ህፃናትና ታዳጊዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል ብለዋል። በሁሉም አካባቢዎች እየተገነቡ የሚገኙ ስታድየሞች ደረጃቸው ከፍ ያለና የሀገሪቱን የስፖርት ዘርፍ እድገት ለማላቅ የሚያግዙ እንደሆኑም ገልጸዋል። የዛሬው ምልከታም ለተወካዮች ምክር ቤት የሚቀርቡ የዘርፉን ሪፖርቶች ትክክለኛነት ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል። የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር የሕዝብ ግንኙነት አማካሪ እርዚቅ ኢሣ ፤ የባሕርዳር ስታድየም የፊፉን እና ካፍን መስፈርቶች ማሟላት በሚችል አግባብ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   ስታዲዮሙ እግር ኳስን ጨምሮ ሌሎች 23 የስፖርት ዓይነቶችን ማስተናገድ እንዲችል ሆኖ የጥራት ደረጃውን ጠብቆ በመገንባት ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የስታድየሙ አብዛኛው ስራ እየተጠናቀቀ መሆኑንና ቀሪዎቹን ፈጥኖ ለመፈፀም ርብርብ እየተደረገ መሆኑም ተመላክቷል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና ማሕበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ከስታዲየሙ በተጨማሪ የዕደ ጥበብ ማዕከላት፤ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እንደሚጎበኙ ይጠበቃል፡፡
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ (ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃ ላላት ጽኑ ቁርጠኝነት እውቅና የሰጠ ነው - ኢጋድ
Nov 15, 2025 86
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃና አረንጓዴ ልማት ቁርጠኝነቷ እውቅና የሰጠ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ገለጸ። የድርጅቱ ዋና ጸሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ኮፕ 32 እንድታዘጋጅ መመረጧን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤውን ማዘጋጀቷ በአየር ንብረት እና ልማት ያላት መሪነት እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። የአካባቢ ስነ ምህዳርን ወደ ነበረበት የመመለስ፣ ዘላቂ እድገትና የማይበገር አቅም ለመገንባት ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያመላክትና ለዚህም ስራዋ እውቅና የሰጠ መሆኑን አመልክተዋል። አረንጓዴ ዐሻራ እና የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት ስራ ማሳያዎች እንደሆኑም ነው የተናገሩት። ኮፕ 32 ለኢጋድ ቀጣና ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጸው ተቋሙ ድርቅ፣ የአየር ንብረት ለውጥ የፈጠረው የዜጎች መፈናቀልና የውሃ እጥረትን ጨምሮ ሌሎች አንገብጋቢ አጀንዳዎች የበለጠ ትኩረት እንዲሰጣቸው እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ኢጋድ ከኢትዮጵያ፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ማዕቀፍ ጽህፈት ቤት(UNFCCC Secretariat) እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን ጉባኤው ሁሉን አሳታፊ፣ የአፍሪካ የቅድሚያ ትኩረቶች ማዕከል ያደረገና ለአየር ንብረት ለውጥ ዘላቂ መፍትሄ የሚገኝበት እንዲሆን በትብብር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በብራዚል ቤለም እየተካሄደ የሚገኘው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 30) ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን ኮፕ 32 ጉባኤ እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል። የአፍሪካ ሀገራት ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ሙሉ ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ታሪካዊ ነው - የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር
Nov 15, 2025 95
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ታሪካዊ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀ መንበሩ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ32)ን እንድታስተናግድ በመመረጧ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጉባኤውን የማስተናገድ ውሳኔው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ታሪካዊ መሆኑን ሊቀመንበሩ ገልጸው ይህም አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃ ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አማካኝነት እያሳየች ያለውን የአየር ንብረት የመሪነት ሚናም አድንቀዋል። ኢትዮጵያ መጠነ ሰፊ የደን መልሶ ልማት እና አረንጓዴ ዐሻራን ጨምሮ ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃ እርምጃዎችን እየወሰደች እንደምትገኝ አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በስኬት በማስተናገድ እምቅ አቅም እንዳላት አንስተው ከፍተኛ ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ጉባኤዎችን ለማዘጋጀት ጠንካራ ተቋማዊ አቅም እና ልምድ አላት ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ ጉባኤውን እንድታስተናግድ መመረጧ በዓለም አቀፍ ትብብር ያላትን ማዕከላዊ ሚና የበለጠ እንደሚያሳድገውም ገልጸዋል። ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ማዕቀፍ(UNFCCC) እና አጋሮች ጋር በመሆን(ኮፕ 32) ሁሉን አካታችና ውጤታማ በማድረግ የአፍሪካን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የበለጠ ለማራመድና ዓለም አቀፍ አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። በብራዚል ቤለም እየተካሄደ የሚገኘው 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 30) ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚከናወነውን ኮፕ 32 እንድታስተናግድ ተመርጣለች። የአፍሪካ ሀገራት ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ሙሉ ድጋፋቸውን መስጠታቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ውጤት ለማምጣት ቁርጠኛ ናት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Nov 14, 2025 130
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አረጋገጡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የበጋው ደረቅ፣ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ይቀጥላል
Nov 12, 2025 153
አዲስ አበባ፤ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አስር ቀናት በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የበጋው ደረቅ፣ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፥ በሰሜን፣በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ፣ መካከለኛው እና ደቡብ ደጋማ አካባቢዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ እንደሚቀጥል አስታውቋል። በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑት የደቡብ፣ደቡብ ምስራቅ እና የደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች ያሳሉ ብሏል። ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ በሰሜን፣ መካከለኛው፣ ምዕራብና ደቡብ ጎንደር ዞኖች፣ባህርዳር ዙሪያ፣ አዊ፣ በምዕራብና ምስራቅ ጎጃም፣ መተከል፣ አሶሳ፣ ካማሺ፣አርሲ፣በባሌ ዞኖች አልፎ አልፎ ሊዘንብ እንደሚችል ኢኒስቲትዩቱ ገልጿል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት በደቡብ ምዕራብ እና ደቡባቢ የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚኖረው መካከለኛ መጠን ያለው ርጥበት ለወቅቱ የግብርና ስራ እንቅስቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው አስታውቋል። የበጋ ርጥበት ተጠቃሚ ተፋሰሶች መጠነኛ የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው የሚጠበቅ ሲሆን የተቀሩት ዝቅተኛ ርጥበት እንደሚኖራቸው ገልጿል። በዚህም አብዛኛው ባሮ አኮቦ፣ መካከለኛው እና ታችኛው ኦሞ ጊቤ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ አባይ እንዲሁም ገናሌ ደዋ መካከለኛ ርጥበት ያገኛሉ፡፡ አብዛኛው አዋሽ፣ዋቤ ሸበሌ፣አፋር ደናክል፣ተከዜ፣ ኦጋዴን ደግሞ ከመጠነኛ ርጥበት እስከ ደረቅ ሁኔታ ይኖራቸዋል ተብሏል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 454
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል።   የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 608
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል።   ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል።   ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
Oct 31, 2025 501
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው  
Oct 24, 2025 754
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡   በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡   ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡   በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ሐተታዎች
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 103
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 290
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 359
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 532
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2074
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2326
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3206
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3298
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 1341
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 908
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6746
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5219
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 56536
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51861
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32567
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30078
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26293
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 24946
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24596
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 24543
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 56536
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51861
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32567
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30078
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በጥምር ግብርና ስኬት ያስመዘገቡት አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ
Nov 14, 2025 216
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ - ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ጨዛ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ለዘመናት ባከናወኑት የግብርና ልማት ሥራ ኑሯቸው ከእጅ ወደ አፍ የዘለለ አልነበረም። ዛሬ ላይ ሆነው ያን ዘመንና ያሳለፉትን ዕድሜ ሲያስታውሱ ይቆጫሉ። በኋላ ቀር መንገድ ሲያከናውኑት ከነበረው የግብርና ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ መሆንም፤ ሀብት ማፍራትም ሳይችሉ ቀርተዋል።   አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ይባላሉ። ከሰበሰቡት ሰብል ጎተራቸው ሳይጎድል፣ ከእንስሳት እርባታ ስራቸውም ጥገታቸው ሳትነጥፍ ማየት የዘውትር ህልማቸው ነበር። ለም መሬት ይዘው ምርታማ ባለመሆናቸው ሲቸገሩ፣ የሚሰራ ጉልበት ይዘው ማዕዳቸው እየጎደለ የጎልማሳነት ዕድሜ መባቻ ድረስ ችግር ሲፈራረቅባቸው ዓመታትን አሳልፈዋል። ይህ ፍላጎታቸው ሰምሮ፣ ጓሯቸው ለምቶ፣ ቤታቸው ሞልቶና ጥሪት አፍርተው የማየት ውጥናቸው ሳይሳካ ዓመታት ቢቆጠሩም ዛሬ ግን በጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ነገሮች ተቀይረዋል። የዓመታት ምኞታቸውን ማሳካት ጀምረዋል። ከስድስት ዓመታት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ለስኬት እንዲበቁ ከማድረግ ባለፈ በአካባቢያቸው አርአያ የሆኑ አርሶ አደር አድርጓቸዋል። የጥምር ግብርና ስራቸው ለዓመታት ከነበሩበት ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ በማውጣት ለአፍም ለኪስም ሆኗቸዋል። የመንግስት የልማት ትኩረት የሆነው ጥምር ግብርና በውስን መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅንጅት እንዲያለሙ እድል ፍጥሮላቸዋል። በዋናነት በሰብል፣ በእንሰት፣ በፍራፍሬና በእንስሳት እርባታ ላይ አተኩረው እየሰሩ ይገኛሉ። ይህም የአንዱ ክፍተት በሌላው እየተሞለ ውጤታማ ስላደረጋቸው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው። ለቤት ፍጆታ ብቻ ያመርቱ የነበረው የእንሰት ምርትን በማስፋፋት ችግኙንና ተረፈ ምርቱን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጭምር ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያመርቱት ገብስ ለሌሎች አርሶ አደሮች ምሳሌ መሆን ችለዋል።   ዝርያቸው የተሻሻሉ ላሞችን ስለሚያረቡም ወተት ከማጀታቸው አይጠፋም። በጓሯቸው የሚያለሙትን አትክልትና ፍራፍሬ ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ፈጥረዋል። አርሶ አደሩ ከንብ ማነብ ሥራቸውም እንዲሁ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው። ከአካባቢው ስነምህዳር ምክንያት ብዙም ያልተለመደውን ቡና በመትከል ለፍሬ አብቅተዋል። የእሳቸውን ፈለግ የተከተሉ ሌሎች አርሶ አደሮችም ቡና ማልማት ጀምረዋል። በእጅ ያለን ሀብት ወደ ውጤት ለመቀየር ተግቶ መስራትና ጽናት ያስፈለጋል ያሉት አርሶ አደር ወልዴ፣ በግብርና ባለሙያዎች የተደረገላቸው ሙያዊ ድጋፍና የተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ለውጤታቸው ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የእርሻ ልማትና የእንስሳት እርባታውን በቅንጅት ማከናወናቸውም እንዲሁ። አርሶ አደር ወልዴ የዓመታት ቁጭታቸው ዛሬ መፍትሄ እያገኘ ነው። የጥምር ግብርና ሥራቸው በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉና ልጆቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እንዲያሳድጉ አስችሏቸዋል። መኖሪያ ቤትን ጨምሮ የተለያየ ሀብት ለማፍራት ምክንያት በመሆኑም ልማቱን አስፋፍቶ ለማከናወን አቅደዋል።   አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ጭምር አርአያ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙራዱ ብሩ ናቸው። ቀደም ሲል በገብስ ምርት ላይ ብቻ አተኩረው ይሰሩ የነበረውን የግብርና ሥራ እንዲቀይሩ ምክንያት እንደሆኗቸው ይገልጻሉ። ከአርሶ አደር ወልዴ በወሰዱት ልምድ ወደ ጥምር ግብርና ገብተዋል። በዚህም ድርቅ የመቋቋም አቅም ያለውን እንሰት በማሳቸው በስፋት ማልማት ጀምረዋል። የነበሯቸውን ሀገረሰብ የዳልጋ ከብቶች በተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች በመቀየር የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ተግተው እየሰሩ ነው። ጥምር ግብርና የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ከአርሶ አደር ወልዴ ተምሪያለሁ ይላሉ። ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባለፈ የመሬት ለምነትን ለማስጠበቅም ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ የጀመርነውን ሥራ እናጠናክራለን ሲሉም ነው የገለጹት።   የሙህር አክሊል ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ መኑር ጀማል በበኩላቸው "አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ በውስን መሬት ገብስ፣ እንሰት፣ ቡና እና የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በጥምር በማልማት የራሳቸውን ህይወት ከመቀየር ባለፈ ለሌሎች አርሶ አደሮች አርአያ እየሆኑን ነው ብለዋል። አርሶ አደሩ በሽታ መቋቋም የሚችሉና ለመድሃኒትነት የሚፈለጉ የእንሰት ዝርያዎችን በማፍላት ለገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ። ከዚህም ባለፈ በመጥፋት ላይ የነበሩ የእንሰት ዝርያዎችን የመታደግና የአፈር ለምነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውንም ተናግረዋል፡፡ የጥምር ግብርና አሰራር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ በመሆኑ በወረዳው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት። የአርሶ አደር ወልዴ ልምድን በማስፋት የሌሎች አርሶ አደሮችም ጓዳ ሞልቶ እንዲትረፈረፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጥምር ግብርና አርሶ አደሩ ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ጭምር እንዲተርፍ የማድርጉ ሥራ ይጠናከራል ብለዋል።   ልማቱ እርስ በእርስ የሚደጋገፉና በአንድ መሬት ላይ የተለያዩ ምርቶችን በማግኘት የተሻለ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚሰራው ሥራ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ በጥቂት መሬት ብዙ ማምረት መቻል ነው። በመሆኑም በተለይ የመሬት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በሥራ ውጤታማ ለመሆን ሁሉም ነገር ምቹና አልጋ በአልጋ መሆን የግድ እንዳልሆነ አርሶ አደሩ ጥሩ ማሳያ ናቸው። ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ዕድል እንዴት ወደሀብትነት መቀየር እችላለሁ ብለው ከሰሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ የእሳቸው የስኬት ጉዞ በቂ ማሳያ ነው። ሰርቶ ለመለወጥም ሆነ ሀብት ለማፍራት ችግሮችን በጽናት ማለፍ እና የሥራ ትጋት ወሳኝ ነውና ተሞክሯቸውን ማስፋት ያስፈልጋል።
  "ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ"
Nov 12, 2025 303
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ" ብርሃኑ ፍቃዱ -ከሰቆጣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልካዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረት ያለው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ማብራራታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ የባህር በሯን ያጣችበትን የ30 ዓመታት ታሪክ ለመቀልበስ ይህን ያህል ዓመት እንደማይወስድ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ ሕጋዊና ተቋማዊ መሰረት የሌለው የሚያስቆጭ ብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል ስለመሆኑም አንስተዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ እና አቶ አድማሱ ደሳለኝ፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር የተወለዱበት ስፍራ፣ የኖሩበት ቀዬ፣ ያሳደጋቸው ማህበረሰብ ... የዘመናት ትዝታና ትውስታቸው እንደሆነ ይገልጻሉ። ይህን የታሪካቸው አካል የሆነውን የባሕር በር ማጣትም የሁል ጊዜ ፀፀትና እንደ ሰውነት ጥላ አብሮዋቸው የሚዞር እውነታ ነው። ከአካባቢው ርቆ ለሚገኝ ሰው ትውስታውን ሲያወራ ለሌላው ተረት ተረት፤ ለራስ ደግሞ የውስጥ ቁስል ማገርሸት ሆኖ ነው የሚሰማው ይላሉ።   ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብንና የቀይ ባህር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሸፍጥ ማጣቷ በቀይ ባህር ላይ እየዋኙ፣ ውሃ እየተራጩ፣ በዳርቻው ነፋሻማ ስፍራ እየተዝናኑ... ለኖሩት ለእነ መለሰ እና አድማሱ መቼም የማይረሳ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ለአለም ማሕበረሰብ ጥያቄውን ሲያሳውቁ ተደብቆ ለቆየው ትውስታቸው አዲስ ተስፋ እንደሰጣቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ በአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል ለ12 ዓመታት እንዳገለገሉ በትውስታና ቁጭታቸውን ወደ ኋላ ተመልሰው ያወሳሉ። አሁን በሰቆጣ ከተማ የሚኖሩት አቶ መለሰ ይሄይስ ፤ የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ተደማሪ አቅም ነበር በወቅቱ ይላሉ።   ይህን የአሰብ ወደብንና የቀይ ባሕር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሴራ ኢትዮጵያ ስታጣ ይሰሩበት ከነበረው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ስራ አቁመው ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሰቆጣ መምጣታቸውን አውስተዋል። በራሳቸው ላይ ከደረሰባቸው የስራ እና ሃብትና ንብረት ማጣት ፣ እንግልትና ሌሎች ችግሮች በላይ ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተነጠለችበትን ሁኔታ ሲያስቡና ሲያሰላስሉ እንደሚያስቆጫቸው ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን በማጣት የባሕር በር ብቻ ሳይሆን የገቢና ወጭ ንግድን፣ የነዳጅ ማጣሪያ ጭምር ነው ያጣችው ያሉት አቶ መለሰ፤ አሁን ጥያቄው መነሳቱ ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ ገናናነቷ ለመመለስ ያለመ አበረታች ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። መንግስት ያነሳው የባሕር በር ጥያቄም የዘመናት ቁጭታችንን፣ ብስጭታችንን እና ህልማችንን ከተደበቀ ትውስታ፤ ወደ አዲስ ተስፋ የወሰደ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ህጋዊና ታሪካዊ ነው ያሉት አቶ መለሰ ፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝም ለአዲሱ ትውልድ በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።   ከ1973 ዓ.ም ጀምረው ለአስር ተከታታይ ዓመታት በአሰብ ወደብ የሲቪል መሃንዲስ ክፍል ሰራተኛ እንደነበሩ ያወሱት አቶ አድማሱ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የባሕር ባር ባለቤት በሆነችባቸው ዘመናት ገናና እና የተከበረች ሀገር ሆና መቆየቷን አንስተዋል። የባሕር በሩ የኢትዮጵያ የገቢና ወጭ ንግድ የሚሳለጥበት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሄን ታላቅ ትሩፋትና ፀጋ ለማስመለስ የተጀመረው እንቅስቃሴ ቁጭትና ትውስታችንን ወደ አዲስ ተስፋ የቀየረ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪካዊ ጠላቶችና ባንዳዎች እኩይ ሴራ የባሕር በር ካጣች ወዲህ ጥያቄውን ማንሳት የማይቻልበት የአፈናው ዘመን አክትሞ በለውጡ መንግስት መነሳቱ አበረታችና ለማስመለስም ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። እኔም ባለኝ አቅም ሁሉ ስለባሕር ባር አስፈላጊነት፣ ጥቅምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ለስኬታማነቱ የድርሻዬ እወጣለሁ ሲሉም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም