ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
አዲሱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዓለምን የማስተሳሰር አቅም የሚጨምር ነው- የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ
Nov 3, 2025 31
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ በቢሾፍቱ የሚገነባው አዲሱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዓለምን የማስተሳሰር አቅም የማጠናከር ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ አለው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገለጹ። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ ተጀምሯል። የፎረሙ አካል የሆነ እና በቢሾፍቱ በሚገነባው አዲስ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ግንባታ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል። በውይይቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ የአየር ማረፊያው ግንባታ አጋር የሆነው ዓለም አቀፉ አማካሪ ድርጅት ዳር አል-ሃንዳሳህ እና የግንባታው ከፍተኛ አማካሪ የሆነው ዓለም አቀፍ ተቋም ኬፒኤምጂ ተወካዮች ተገኝተዋል። አየር ማረፊያው ከአውሮፓ ኩባንያዎች ጋር ኢንቨስትመንት እና አጋርነት የሚፈጥር ትልቅ እድል መሆኑ ተገልጿል። የገንዘብ ሚኒስትሩ ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ የሚገነባው አየር ማረፊያ ለውጥ ለማምጣት፣ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እና ዓለም አቀፍ ትስስርን ለማጠናከር ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። የኤርባስ የአፍሪካ ኃላፊ ፌዴሪኮ ቡልቶ ኩባንያው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሻ ገልጸዋል። የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደ ኤምሬትስ እና ኳታር አየር መንገዶች ዓለምን የማስተሳሰር ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርለት ተናግረዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች የአየር ማረፊያ ግንባታውን አስመልክቶ ጠቃሚ ግንዛቤ ማግኘታቸው ተገልጿል። የአውሮፓ ባለሀብቶች በአየር ማረፊያው ግንባታ ለመሳተፍ ፍላጎት ያሳዩበት መድረክ መሆኑንም የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 23
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
በፕሪሚየር ሊጉ ሸገር ከተማ እና ሃዋሳ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል
Nov 3, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአራተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ተካሄደዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን በያሬድ መኮንን ግብ 1 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎ ሸገር ከተማ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን ሲያስመዘግብ ቅዱስ ጊዮርጊስ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ሽንፈቱን አስተናግዷል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታን 3 ለ 1 ረቷል። ጌታነህ ከበደ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ያሬድ ብሩክ ቀሪዋን ጎል ለሃዋሳ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሱሌይማን ሃሚድ ለመቀሌ 70 እንደርታ ብቸኛዋን ጎል ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ሃዋሳ ከተማ በሊጉ ሶስተኛ ድሉን ሲያስመዘግብ በተቃራኒው መቀሌ 70 እንደርታ ሶስተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል። ዛሬ አስቀድሞ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸንፏል።
በመካከለኛው፣ምስራቅ እና የደቡባዊ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ እየጨመረ ይሄዳል
Nov 3, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦በመካከለኛው፣ምስራቅ እና የደቡባዊ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ እንደሚሄድ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በመካከለኛው፣ምስራቅ እና የደቡባዊ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች የአየሩ ሁኔታ እንደሚቀያየር አስታውቋል። በደብረ ብርሃን፣አርሲ ሮቤ፣አዳባ፣ደሴ፣ባሌ ሮቤ፣አዲስ አበባ፣አደሌ፣አምባ ማሪያም፣ ኮምቦልቻ፣ አንኮበር በአብዛኛው ቀናቶች ላይ ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየስ በታች እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል። የበጋ ወቅት ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑት የደቡብ፣ደቡብ ምዕራብና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚቀጥሉት አስር ቀናት ዝናብ ያገኛሉ ተብሏል። በሌላ በኩል አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የበጋው ደረቅ፣ጸሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ተጠናክሮ ይቀጥላል። በመካከለኛው፣የምስራቅ እና ደቡብ ደጋማ ቦታዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ እንደሚሄድ የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል። ደቡብ ምዕራብ፣ ደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራቸዋል። የመኽር ሰብል አብቃይ በሆኑት የደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች በወሩ ያለው እርጥበት ዘግይተው ለተዘሩት፣ የእድገት ጊዜያቸውን ላልጨረሱ ሰብሎች፣ለቋሚ ተክሎችና ፍራፍሬዎች የውሃ ፍላጎት ለማሟላት ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ገልጿል። ያለው እርጥበት ለእንስሳት መኖም አዎንታዊ አበርክቶ እንዳለው ጠቁሟል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበጋ እርጥበት ተጠቃሚ ተፋሰሶች ላይ የተሻለ የገጸ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው የሚጠበቅ ሲሆን የተቀሩት ተፋሰሶች ዝቅተኛ እርጥበት እንደሚኖራቸው ትንበያው ያሳያል ብሏል። አብዛኛው የባሮ አኮቦ፣ኦሞ ጊቤ፣ገናሌ ዳዋ፣ኦጋዴን፣ በመካከለኛው እና በታችኛው ስምጥ ሸለቆ፣ዋቤ ሸበሌ የተሻለ የገጸ ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው ጠቁሟል። አብዛኛው አፋር ደናክል፣አዋሽ፣ተከዜ፣መረብ ጋሽ እንዲሁም አይሻ ተፋሰሶች ላይ ደረቅ የአየር ሁኔታ ጠባይ ተጽዕኖ ስር እንደሚወድቁ የአየር ትንበያ ያሳያል ብሏል።
ተፈጥሮ ተኮር የቱሪዝም ልማት ሥራዎችን ማስፋት የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ ነው
Nov 3, 2025 83
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ተፈጥሮ ተኮር የቱሪዝም ልማት ሥራዎችን ማስፋት የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። ከአስር ዓመታት በፊት የተቋቋመው የዓለም የዱር እንስሳት ፕሮግራም ዓመታዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በጉባኤው ከ30 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የዱር እንስሳት ጥበቃ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ለተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ልዩ ትኩረት በመስጠት አበረታች ውጤቶች አግኝታለች። ቀደም ሲል በታሪክና ባህል ተኮር ቦታዎች ላይ ሰፋፊ የቱሪዝም መዳረሻ ልማት ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን አንስተው፤ ይህ ተግባርም የአካባቢው ማህበረሰብ ኑሮ እንዲሻሻል፣ የስራ እድል እንዲፈጠር እና የውጭ ምንዛሬ እንዲገኝ ማስቻሉን ተናግረዋል። በአሁን ወቅት ከቀድሞዎቹ መዳረሻዎች በተጨማሪ የተፈጥሮ ሀብትና ብሔራዊ ፓርኮችን ለቱሪዝም ልማት የማዋል ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ ብሔራዊ ፓርኮችንና የዱር እንስሳት ልማትን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አንስተው፤ ይህም በኢኮ ቱሪዝም በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑና ለተፈጥሮ ሀብትና ለዱር እንስሳት ጥበቃ ተስማሚ ከባቢ ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣይም ተፈጥሮ ተኮር ቱሪዝምን የበለጠ ለማስፋት በትኩረት እንደምትሰራ ተናግረዋል፡። በተለይም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ የተፈጥሮ ሀብቶች ባሉባቸው ቦታዎች ላይ የቱሪዝም ልማቱን ለማስፋት ስትራቴጂዎች ተቀርጸው እየተተገበሩ መሆኑን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃን ለማጠናከር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያከናወነቻቸውን ተግባራት በጉባኤው ላይ በተሞክሮ ታቀርባለች ብለዋል። የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸውን የስንቅሌ ቆርኬዎችን በሃገር በቀል ዕውቀት ቁጥራቸው እንዲጨምር ማድረግ መቻሉን እና ይህንንም ልምዷን ለሌሎች ሃገራት ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ ተመራማሪ አቶ ፋኑኤል ከበደ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ለምታከናውናቸው ተግባራት ከዓለም አቀፉ የዱር ሕይወት መርሃ ግብር ድጋፍ እየተደረገላት ነው ብለዋል። በመርሃ ግብሩ በኢትዮጵያ በአስር ጥብቅ የተፈጥሮ ቦታዎች ላይ ጥበቃ ማድረግ የሚያስችል የ12 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር የሰባት ዓመታት ፕሮጀክት ይፋ መደረጉንም አንስተዋል። በፕሮጀክቱ ጥበቃ ከሚደረግባቸው ቦታዎች፣ ባቢሌ፣ ጨበራ ጩርጩራ፣ ኦሞና ማጎ ብሄራዊ ፓርኮች እና ጉራ ፈርዳ ጥብቅ ደን ይገኙበታል። የተፈጥሮ ሃብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራውም ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን እየተከናወነ ነው ብለዋል።
ፖለቲካ
የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት ለማስከበር የሚያስችል የተሟላ ዝግጁነት እና አቅም ያለው ሰራዊት ተገንብቷል- ሜጀር ጀነራል አዳምነህ መንግስቴ
Nov 3, 2025 75
ጅማ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት ለማስከበር የሚያስችል የተሟላ ዝግጁነት እና አቅም ያለው ሰራዊት መገንባቱን የሀገር የመከላከያ ሰራዊት የሰላም ማስከበር ማእከል ኃላፊ ሜጀር ጀነራል አዳምነህ መንግስቴ ገለጹ። የዳሎል ማዕከላዊ እዝ አባላት እና የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች "እንዳይደገም መቼም አንረሳውም" በሚል መሪ ሃሳብ የጥቅምት 24ቱን ጥቃት በተለያዩ ዝግጅቶች አስበውታል። በዚሁ ሁነት ላይ የተገኙት በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰላም ማስከበር ማእከል ሃላፊ ሜጀር ጀነራል አዳምነህ መንግስቴ፤ መከላከያ ሰራዊት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት ለማስከበር የሚያስችል ዝግጁነትና የተሟላ አቅም የገነባ መሆኑን ገልጸዋል። የሰራዊቱ ወትሮ ዝግጁነትና የግዳጅ አፈፃፀም ብቃት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ከሀገርም ባለፈ ለሌሎች ሃገራት የጀግንነት መገለጫ እና የሰላም ተምሳሌት የሆነ ብቁ ሰራዊት ተገንብቷል ብለዋል። የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት ለማስከበር የሚያስችል የተሟላ ዝግጁነትና ጠንካራ አቅም ያዳበረ ሰራዊት መገንባቱን አንስተው ለማንኛውም ግዳጅ ሰራዊቱ ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል። የዳሎል ማእከላዊ እዝ አባላትም በተሰማሩበት የግዳጅ ቀጣና ሁሉ በጀግንነት ውጤታማ ተልእኮዎችን በመፈፀም የሚታወቁ መሆኑን አንስተው ይህንኑ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። የዳሎል ማእከላዊ እዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ በበኩላቸው ጥቅምት 24ን ማስታወስ ያስፈለገው ሰራዊቱ ለሀገር የከፈለውን መስዋእትነት ለማሳየትና መሰል ጥፋቶች በቀጣይ እንዳይደገሙ ትውልዱ እንዲማርበት በማሰብ ነው ብለዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለሀገር አንድነት እና ሰላም መረጋገጥ በጽናትና በጀግንነት መቆሙን ገልጸው ለቀጣይም የላቀ ዝግጁነት ያለው መሆኑን አረጋግጠዋል። በዚሁ መድረክ ላይ የውይይት መነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት በጅማ ዩኒቨርስቲ የታሪክ መምህር ንጉሱ አደም (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጀግንነት ጸንቶ የቆመ፣ የሀገር ህልውና መሰረት ብሎም የዓለም የሰላም ማስከበር ተምሳሌት መሆኑን አንስተዋል። የሀገሩን ዳር ድንበር ከማስከበር አልፎ በተለያዩ ሃገራት በሰላም ማስከበር ተልእኮ የተመሰከረለት ጠንካራ ሰራዊት መሆኑን አስታውሰው በዚህም ክብርና አድናቆት ሊቸረው ይገባል ብለዋል። በጅማ ከተማ በተካሄደው መርሀ ግብር ላይ የሰራዊቱ አባላትና ከፍተኛ መኮንኖች፣ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ ምሁራን፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶችና የተለያዩ የማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።
የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ተዘጋጅተናል- ሰልጣኝ የሕግ አስከባሪዎች
Nov 3, 2025 94
ገንዳ ውኃ፤ ጥቅምት 24/2018 (ኢዜአ):-የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት መዘጋጀታቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን የተመደቡ አዲስ የአድማ መከላከልና መደበኛ ፖሊስ አባላት ገለጹ። ሰልጣኝ የሕግ አስከባሪዎቹ ወደ ዞኑ ሲገቡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ከሰልጣኞቹ መካከልም የአድማ መከላከል ፖሊስ ሙሐመድ ሱሌማን በሰጠው አስተያየት፤ ሀገርንና ሕዝብን ለማገልገል በነበረው ፍላጎት ወደ ፖሊስ ተቋም በመቀላቀል ተገቢውን ፖሊሳዊ ስልጠና መውሰዱን ተናግሯል። በስልጠና ቆይታው ያገኘውን እውቀትና ፖሊሳዊ ጥበብ በመጠቀም የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የድርሻውን ለመወጣት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል። ኮንስታብል ዳዊት ሞላ በበኩሉ፤ የተሰጠውን ሀገራዊና ሕዝባዊ አደራ ለመወጣት አበክሮ እንደሚሰራ ገልፆ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩሉን ሚና በመወጣት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ እንደሚተጋ ተናግሯል። ሰልጣኞቹ የተጣለባቸውን ሕዝባዊ አደራ ታማኝነትን በጠበቀ አግባብ ለመወጣት መዘጋጀታቸውንም አረጋግጠዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ ተወካይና የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ መሰንበት መልካሙ እንደገለጹት፤ ሰልጣኝ የሕግ አስከባሪዎች ሰላምን ለማፅናት በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ተገቢው ድጋፍና ክትትል ይደረጋል። የዞኑ ሕዝብ ሰላም ወዳድና የልማት አርበኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሕብረተሰቡ ለፀጥታ አካሉ ተልዕኮ ስኬታማነት እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል። መከላከያ ሰራዊት የ504ኛ ኮር ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ቾምቤ ወርቁ በበኩላቸው፤ ሰራዊቱና የክልሉ የፀጥታ ኃይል የጥፋት ኃይሎችን ተልዕኮ በቅንጅት በማምከን አኩሪ ገድል እየፈፀሙ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ሰላምን የማፅናትና የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ ተግባር እንደ ሁልጊዜው ሁሉ በቀጣይም በሕዝቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
የባንዳ ስራ ላይ የተሰማሩ ኃይሎች ከሀገር ክህደት ተግባራቸው ሊቆጠቡ ይገባል - ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
Nov 3, 2025 127
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ የባንዳ ስራ ላይ የተሰማሩ ኃይሎች ከሀገር ክህደት ተግባራቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ገለጹ። የመከላከያ ሰራዊት የሰሜን ዕዝ ጥቃት የሚዘከረው የተፈጸመው አሳዛኝ ድርጊት መቼም እንዳይደገም ለማስታወስ መሆኑንም የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ገልጸዋል። የመከላለከያ ሰራዊት የሰሜን ዕዝ የተፈጸመበት ጥቃት አምስተኛ ዓመት ዝክረ ሰሜን ዕዝ "እንዳይደገም መቼም አንረሳውም" በሚል መሪ ሀሳብ በቢሾፍቱ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ተከብሯል። ከአምስት ዓመት በፊት ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም የጀግናው መከላከያ ሰራዊት አካል የሰሜን ዕዝ ክህደት እንደተፈፀመበት ይታወቃል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፣ የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰና ሌሎች ከፍተኛ ጄኔራል መኮንኖችና የመከላከያ ሰራዊት አባላት ተገኝተዋል። የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ጥቅምት 24 ቀን የሰሜን ዕዝ ዝክረ ሰማዕታት ቀን ነው። የመከላከያ ሰራዊት የሀገሩን ዳር ዳር ድንበር በማስከበር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆኑንም አውስተዋል። የሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ለትግራይ ክልል ምሽግና አጥር እንደነበር ገልጸው፤ እስከ አሁን ከሰሜን ዕዝ ውጪ በራሱ ዜጎች ጥቃት የደረሰበት አጋጣሚ እንዳልተፈጠረ ተናግረዋል። የመከላከያ ሰራዊት ከራሱ ቀንሶ በትግራይ ብዙ ትምህርት ቤት፣ ጤና ተቋማትና የግብርና ልማት እንዳከናወነ ገልጸው፣ ጥቅምት 24 ቀን የተፈጸመው ድርጊት ግን በኢትዮጵያ ታሪክ ጥቁር ነጥብ ነው ብለዋል። የሰሜን ዕዝ ጥቃት መቼም እንደማይረሳ ገልጸው፤ ቀኑ የሚዘከረው መቼም እንዳይደገም መሆኑን አንስተዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ዕለቱን ሲያስታውሱ፤ መንግሥት በወቅቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተለኮሱ ግጭቶችን ለማብረድ የሚታትርበት እንጂ የጦርነት ዝግጁነት እንዳልነበረው አውስተዋል። መንግሥት ሁልጊዜም ለሰላማዊ መንገድ በሩን ክፍት ማድረጉን ጠቁመው፤ ከትላንት ባለመማር የሚደረግ ፉከራ መቆም አለበት ብለዋል። የቀድሞው ህወሓት ጥቂት አባላት የታጠቁ ኃይሎችን በመደገፍ፣ ሀገር ለማፍረስ ከጎረቤት ሀገር ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ በዲ.ዲ.አር የተሰባሰቡትን በመበተን የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት እየጣሱ መሆኑንም ገልጸዋል። የባንዳ ስራ ላይ የተሰማሩ እነዚህ ህዝቡን የማይወክሉ ኃይሎች ከሀገር ክህደት ተግባራቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባም ተናግረዋል። የመከላከያ ሰራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን በበኩላቸው፤ ከአምስት ዓመት በፊት በሰሜን ዕዝ የሰራዊት አባላት ላይ የተፈፀመው ጥቃት በሀገር ሉዓላዊነት ላይ የተቃጣ ደባ መሆኑን ጠቁመዋል። ዝክረ ሰሜን ዕዝ ወቅቱን በሚመጥን መልኩ እየተከበረ ነው ብለዋል። የተፈጸመው ጥቃት እንዳይደገም መቼም አንረሳውም ያሉት ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው፣ ጥቃቱን ለመመከት ሲሉ መስዋዕትነት የከፈሉ የሰራዊቱ አባላትን ለማስታወስ እና ለተጋድሏቸው ዕውቅና ለመስጠት እንደሚዘከር ገልጸዋል።
ከምክር ቤቱ የመጨረሻ ዓመት የሥራ ዘመን ምን ይጠበቃል?
Nov 3, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ ከ6ኛው ዙር ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመጨረሻ ዓመት የሥራ ዘመን የሚጠበቁ ጉዳዮች ምንድ ናቸው? 6ኛው ዙር የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመን ዘንድሮ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። ምክር ቤቱ በሕገ-መንግስቱ በተሰጠው ሥልጣንና ተግባር መሰረት ሕግ ያወጣል፣አስፈጻሚ ተቋማትን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል። የፓርላማ ዲፕሎማሲ እንዲሁም የህዝብ ውክልና ሥራዎችን ያከናውናል። ምክር ቤቱ ባለፉት አራት ዓመታት ሀገራዊ ለውጡን የበለጠ የሚያሳልጡና የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚመልሱ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን የምክር ቤቱ አባላት ያነሳሉ። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የምክር ቤቱ አባላት በቀሪ የሥራ ጊዜያቸው የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች የበለጠ ውጤታማ እንዲሆኑ በትጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) በተያዘው ዓመት ከሚጠበቁ ጉዳዮች መካከል ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በተመረጡ አጀንዳዎች ላይ የሚያደርገው ውይይት ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሥብራት ለመጠገንና ነባር ችግሮችን በምክክር የመፍታት ባህል ለማዳበር መፍትሄ እንደሚያመጣ እንደታመነበትም ነው ያነሱት። ምክር ቤቱ በቀሪ የሥራ ዘመኑ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባና ችግሮች በምክክር መፍትሄ እንዲያገኙ አበክሮ ይሰራል ብለዋል። የፓርላማ ወዳጅነት ቡድኖች ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰሩ የገለጹት ደግሞ ሌላው የምክር ቤት አባል ሳዲቅ አደም ናቸው። በፓርላማ ዲፕሎማሲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች የሚያስከብሩና የሀገሪቷን የልማት ፍላጎትን የሚያስረዱ ጉዳዮች ላይ በስፋት ይሰራል ብለዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው በተያዘው በጀት ዓመት በኢትዮጵያ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን አስታውሰዋል። የምክር ቤቱ አባላትም በመጨረሻ ዓመት የሥራ ጊዜያቸው እነዚህ ፕሮጀክቶች በተሻለ ፍጥነትና ፈጠራ እውን እንዲሆኑ የተለየ ድጋፍና ክትትል ያደርጋሉ ብለዋል። ለሚቀጥለው ምክር ቤት አስቻይ ሁኔታዎችን ማመቻቸት የ5ኛ ዓመት የምክር ቤት አባላት ድርሻ መሆኑንም አንስተዋል።
የጎንደር ከተማ ነጋዴዎች ለከተማቸው እድገትና ሰላም መስፈን በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እየተወጡ ነው
Nov 2, 2025 239
ጎንደር ፤ ጥቅምት 23/2018 (ኢዜአ):-ለጎንደር ከተማ እድገትና ሰላምን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን በጎንደር ከተማ የንግዱ ማህብረሰብ አባላት ገለጹ፡፡ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችና በአካባቢ ሰላምና ልማት ዙሪያ የከተማው የንግዱ ማህበረሰብ የምክክር መድረክ ዛሬ አካሂደዋል፡፡ ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ አብዱራህማን ሰኢድ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች ዳር እንዲደርሱና ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። በተለይም በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም ለማጽናትና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት መሳተፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ተሾመ ንጉሱ በበኩላቸው እንደ አንድ የንግዱ ማህበረሰብ አባል ህብረተሰቡን የሚያማርሩ ህገወጦችን በማጋለጥ መንግስት ለሰላም መስፈን የሚያደርገውን ጥረት ይበልጥ ለማገዝ እንደሚተጉ አስረድተዋል። የንግዱ ማህበረሰብ የግብር ግዴታውን በመወጣት ለሀገር እድገት የሚያበረክተውን ሚና ማጠናከር እንደሚገባውም ጠቁመዋል። በምንከፍለው ግብር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን በማየታችን ተደስተናል፤ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የድርሻዬን ለማበርከት ዝግጁ ነኝ ያሉት ደግሞ አቶ ጀማል ቃሲም ናቸው፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ጥሩዬ አታክልት እንደገለጹት በከተማው ሰላም መረጋገጡ የንግድ እንቅስቃሴው እንዲነቃቃ አስችሏል። ይህም የንግዱ ማህበረሰብ ሰርቶ በሚያገኘው ልክ የመንግስትን ግብር በታማኝነትና በወቅቱ እንዲከፍል ምቹ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ የንግዱ ማህበሰረብም በሰላም ግንባታ እያበረከተ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡ በምክክር መድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ከስድስት ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የሰላምን አማራጭ ያልተከተሉ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት ዝግጁ መሆን አለባቸው
Nov 2, 2025 252
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 23/2018 (ኢዜአ):- የሰላምን አማራጭ ያልተከተሉ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተናገሩ፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ወቅት እንዳረጋገጡት፤ መንግሥት ወደ ሰላም ከሚመጣ የትኛውም ኃይል ጋር ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን አብሮ ለመስራት ሁል ጊዜም ዝግጁ ነው። በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ የሚስተዋሉ የሰላምና የፀጥታ ችግሮች በዘላቂነት እንዲፈቱ መንግሥት ሰላምን ቀዳሚ አማራጭ አድርጎ እየሠራ መሆኑንም ነው የተናገሩት። መንግስት ሁሌም የሰላም መንገድ ከሚመርጡት ጋር ለመነጋገር ዝግጁ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጠው፤ በአገር ፍላጎት እስከ ተግባባን ድረስ የግል ጉዳይን መተው አስፈላጊ ነው ብለዋል። አሁንም ለሰላም በራችን ክፍት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ካልተደመርንና ካልተጋገዝን የኢትዮጵያን ችግሮች በአጭር ጊዜ ልንፈታ እንደማንችል በመገንዘብ በሰላማዊ መንገድ አብሮ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር)፤ችግሮችን በውይይት መፍታት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ነው ብለዋል። መንግስት ለታጠቁ ኃይሎች ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪዎችን እያቀረበ መሆኑን ገልጸው፤ ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሰላማዊ አማራጭ የመጡ በርካታ ወገኖች መኖራቸውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ አሁን ላይ በፈጣን ዕድገት ላይ እንደምትገኝ ጠቁመው፤ ሀገሪቷ ከምታደርገው የዕድገት ግስጋሴ የሚያስተጓጉላት ነገር ባለመኖሩ ታጣቂዎች ግብ ለሌለው ትግል ጊዜያቸውን ማባከን እንደሌለባቸው አብራርተዋል። መንግስት ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እና ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። በምክክሩ ማንኛውም አካል አለኝ የሚለውን ጥያቄ በማቅረብ በሰላማዊ መንገድ መወያየት እንደሚችል አመልክተዋል። ሌላኛዋ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አስቴር ከፍታው በበኩላቸው፤ አሁን ላይ ቡድኖችንም ሆነ ግለሰቦችን ለትጥቅ ትግል የሚዳርግ ምንም ሁኔታ እንደሌለ ገልጸዋል። የፖለቲካ ልዩነት ያላቸውም ሆኑ የታጠቁ ኃይሎች ለሰላማዊ ውይይት ቅድሚያ በመስጠት ለዘላቂ ሰላም እውን መሆን የበኩላቸውን ድርሻ ማበርከት እንዳለባቸው ተናግረዋል። በትጥቅ የተደገፈ ትግል ሲያደርጉ የነበሩ ኃይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው በመግባት በልዩ ልዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው አገራቸውንና ህዝባቸውን እያገለገሉ ይገኛሉ።
እየተከናወነ ባለው የሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፏችንን ይበልጥ እናጠናክራለን - የባሕርዳር ወጣቶችና ሴቶች
Oct 31, 2025 336
ባሕር ዳር፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፡- በከተማው እየተከናወነ በሚገኘው የሰላም ግንባታና የልማት ተግባራት ላይ ተሳትፏቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የባሕርዳር ከተማ ወጣቶችና ሴቶች ተናገሩ። የከተማው ወጣቶችና ሴቶች በሰላም ማፅናት ዙሪያ ዛሬ በባሕርዳር ከተማ ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊ ትዕግስት አባቡ በሰጠችው አስተያየት፤ መንግስት ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት በማብቃት የሚደነቅ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብላለች። የልማት ስራዎቹ የወጣቶችንና ሴቶችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ጠቅሳ፤ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አንስታለች። ለልማት ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላም ግንባታ ተሳትፎዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል ተናግራለች። ሌላው ተሳታፊ አዲሱ ዳኘው በበኩሉ፤ ከለውጡ ወዲህ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የወጣቶችና ሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ምቹ መደላደል የፈጠሩ ናቸው ብሏል። እየተከናወኑ የሚገኙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሃገሪቱን ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ደረጃ የሚያሸጋገሩ እንደሆኑም ተናግሯል። የልማት ስራዎቹ የተከናወኑት ከሰላም ግንባታ ጎን ለጎን መሆኑን ጠቅሶ፤ የልማት ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲቻል ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጿል። የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ሃላፊ ቶማስ ታምሩ፤ ከለውጡ ወዲሕ በከተማው የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተለይም ከተማዋን ለቱሪስቶችና ነዋሪዎች ምቹ በማድረግ በኩል የኮሪደር ልማት ስራው ለአብነት የሚጠቀስ ዋና ተግባር ነው ብለዋል። ሌሎች የሕዝብ ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ለዚህም የከተማው ወጣቶችና ሴቶች ድጋፍና ትብብር የጎላ መሆኑን አንስተዋል። የተጀመሩ የልማት ስራዎች የወጣቶችንና የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ተጠቃሚነት የበለጠ እንዲያሳድጉ የሰላም መፅናት ወሳኝ በመሆኑ ሴቶችና ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው አፅንኦት ሰጥተዋል። በከተማ አስተዳደሩ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር ዓይን ገላጭ የሆኑ አበረታች የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች፣ ሕፃናትና ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ ሰብለ ዘውዱ ናቸው። ከተማዋ በተፈጥሮ ያላትን ፀጋ በኮሪደር ልማት በማጉላት ከጣና ሃይቅ ጋር ያላት ትስስር ላቅ ወዳለ ደረጃ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ የልማት ተግባራት እንዲሳኩ የበኩላችንን እንወጣለን -ወጣቶች
Oct 31, 2025 264
ደሴ/ወልድያ/ ሰቆጣ፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፡- የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ የልማት ተግባራት ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚወጡ በአማራ ክልል ወጣቶች ገለጹ። "ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ወጣቶች የተሳተፉባቸው የውይይት መድረኮች በደሴ፣ ወልዲያና ሰቆጣ ከተሞች ዛሬ ተካሂደዋል። ከደሴው መድረክ ተሳታፊዎች ውስጥ ወጣት ከድር የሱፍ በሰጠው አስተያየት፤ መንግስት ሰላምን ከማፅናት ጎን ለጎን የሚያካሂዳቸው ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለወጣቶችና ለቀጣዩ ትውልድም ተስፋ የሰጡ ናቸው ብሏል። ፕሮጀክቶቹ የሀገሪቱን እድገት በማፋጠን መሰረታዊ ለወጥ የሚያመጡ መሆናቸውን ጠቅሶ፤ ከሌሎች ወጣቶች ጋር በመተባበር ሰላም በማስጠበቅ ለአካባቢው ልማት ብሎም ለሀገራዊ ፕሮጀክቶች ስኬታማነት የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ሌላዋ የመድረኩ ተሳታፊ ወጣት ቤተልሔም ፈንታው በበኩሏ፣ የማዳበሪያ፣ የጋዝ፣ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያና ሌሎች ፕሮጀክቶች መገንባት ለመጪው ትውልድ ትልቅ ተስፋ የሰነቁ ናቸው ብላለች። በዚህ ሂደት ፕሮጀክቶቹ ተሳክተው የሀገራችንን ብልጽግና ለማረጋገጥ የድርሻችንን ለመወጣት ቁርጠኛ ነን፤ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጅት ሰላማችንን ለማጽናት የጀመርነውን ስራ እናስቀጥላለን ብላለች። የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተወካይና የሕዝብ ግንኙነት ምክትል አማካሪ አቶ አወል አህመድ በበኩላቸው፤ የከተማውን ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ ከወጣቱ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የወል ትርክትን በማስፈን ሕብረብሔራዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ወጣቶች የጀመሩትን የነቃ ተሳትፎ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በተመሳሳይ በወልዲያው መድረክ ከተሳተፉት መካከል ወጣት አቤል አያሌው፤ የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ ልማት ይበልጥ እንዲጠናከር የድርሻችንን ለመወጣት መንቀሳቀስ አለብን ብሏል። ሰላምን በማፅናት የአካባቢውና ሀገራዊ ተስፋ ሰጪ የልማት ተግባራት ከፍጻሜ እንዲደርሱ በጋራ መነሳት አለብን ያለው ደግሞ ወጣት ኃይለማሪያም ስዩም ነው። የወልድያ ከተማ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሀላፊ አቶ መላኩ ዓለሙ፤ ጽንፈኛ ቡድኑ የባዕዳን ተላላኪ በመሆን ታሪክ የማይረሳው አፍራሽ ድርጊት ለመፈፀም ቢሞክርም በፀጥታ ሀይሉ እየመከነበት በመበታተን ላይ መሆኑን አብራርተዋል። ሰላምን በዘላቂት አፅንቶ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት ወጣቶች ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል። በሌላ በኩል በሰቆጣው ውይይት የተሳተፈው ወጣት ጥላሁን አበበ፤ መንግስት ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ እያደረገ ያለው ጥረት እንደግፋለን ብሏል። ሌላው ተሳታፊ ወጣት አስፋው ገብረ መድህን በበኩሉ፤ ለሰላም መስፈን እኛም ከመንግስት ጎን ተሰልፈን የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉ ገልጿል። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ በበኩላቸው፤ በአካባቢ የሰፈነውን ሰላም አስጠብቆ በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ብሎም የፀጥታ አካላት እያደረጉት ያለው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገራችን ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች ላይ አተኩራለች ያሉት አቶ ጌትነት፤ በቀጣናው ያላትን ተሰሚነት ለማጠናከር ወጣቶች ሚናቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል። በከተሞቹ በተካሄደው የውይይት መድረኮች የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ ወጣቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ፖለቲካ
የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት ለማስከበር የሚያስችል የተሟላ ዝግጁነት እና አቅም ያለው ሰራዊት ተገንብቷል- ሜጀር ጀነራል አዳምነህ መንግስቴ
Nov 3, 2025 75
ጅማ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት ለማስከበር የሚያስችል የተሟላ ዝግጁነት እና አቅም ያለው ሰራዊት መገንባቱን የሀገር የመከላከያ ሰራዊት የሰላም ማስከበር ማእከል ኃላፊ ሜጀር ጀነራል አዳምነህ መንግስቴ ገለጹ። የዳሎል ማዕከላዊ እዝ አባላት እና የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች "እንዳይደገም መቼም አንረሳውም" በሚል መሪ ሃሳብ የጥቅምት 24ቱን ጥቃት በተለያዩ ዝግጅቶች አስበውታል። በዚሁ ሁነት ላይ የተገኙት በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰላም ማስከበር ማእከል ሃላፊ ሜጀር ጀነራል አዳምነህ መንግስቴ፤ መከላከያ ሰራዊት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት ለማስከበር የሚያስችል ዝግጁነትና የተሟላ አቅም የገነባ መሆኑን ገልጸዋል። የሰራዊቱ ወትሮ ዝግጁነትና የግዳጅ አፈፃፀም ብቃት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ከሀገርም ባለፈ ለሌሎች ሃገራት የጀግንነት መገለጫ እና የሰላም ተምሳሌት የሆነ ብቁ ሰራዊት ተገንብቷል ብለዋል። የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት ለማስከበር የሚያስችል የተሟላ ዝግጁነትና ጠንካራ አቅም ያዳበረ ሰራዊት መገንባቱን አንስተው ለማንኛውም ግዳጅ ሰራዊቱ ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል። የዳሎል ማእከላዊ እዝ አባላትም በተሰማሩበት የግዳጅ ቀጣና ሁሉ በጀግንነት ውጤታማ ተልእኮዎችን በመፈፀም የሚታወቁ መሆኑን አንስተው ይህንኑ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። የዳሎል ማእከላዊ እዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ በበኩላቸው ጥቅምት 24ን ማስታወስ ያስፈለገው ሰራዊቱ ለሀገር የከፈለውን መስዋእትነት ለማሳየትና መሰል ጥፋቶች በቀጣይ እንዳይደገሙ ትውልዱ እንዲማርበት በማሰብ ነው ብለዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለሀገር አንድነት እና ሰላም መረጋገጥ በጽናትና በጀግንነት መቆሙን ገልጸው ለቀጣይም የላቀ ዝግጁነት ያለው መሆኑን አረጋግጠዋል። በዚሁ መድረክ ላይ የውይይት መነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት በጅማ ዩኒቨርስቲ የታሪክ መምህር ንጉሱ አደም (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጀግንነት ጸንቶ የቆመ፣ የሀገር ህልውና መሰረት ብሎም የዓለም የሰላም ማስከበር ተምሳሌት መሆኑን አንስተዋል። የሀገሩን ዳር ድንበር ከማስከበር አልፎ በተለያዩ ሃገራት በሰላም ማስከበር ተልእኮ የተመሰከረለት ጠንካራ ሰራዊት መሆኑን አስታውሰው በዚህም ክብርና አድናቆት ሊቸረው ይገባል ብለዋል። በጅማ ከተማ በተካሄደው መርሀ ግብር ላይ የሰራዊቱ አባላትና ከፍተኛ መኮንኖች፣ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ ምሁራን፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶችና የተለያዩ የማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።
የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ተዘጋጅተናል- ሰልጣኝ የሕግ አስከባሪዎች
Nov 3, 2025 94
ገንዳ ውኃ፤ ጥቅምት 24/2018 (ኢዜአ):-የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት መዘጋጀታቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን የተመደቡ አዲስ የአድማ መከላከልና መደበኛ ፖሊስ አባላት ገለጹ። ሰልጣኝ የሕግ አስከባሪዎቹ ወደ ዞኑ ሲገቡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ከሰልጣኞቹ መካከልም የአድማ መከላከል ፖሊስ ሙሐመድ ሱሌማን በሰጠው አስተያየት፤ ሀገርንና ሕዝብን ለማገልገል በነበረው ፍላጎት ወደ ፖሊስ ተቋም በመቀላቀል ተገቢውን ፖሊሳዊ ስልጠና መውሰዱን ተናግሯል። በስልጠና ቆይታው ያገኘውን እውቀትና ፖሊሳዊ ጥበብ በመጠቀም የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የድርሻውን ለመወጣት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል። ኮንስታብል ዳዊት ሞላ በበኩሉ፤ የተሰጠውን ሀገራዊና ሕዝባዊ አደራ ለመወጣት አበክሮ እንደሚሰራ ገልፆ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩሉን ሚና በመወጣት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ እንደሚተጋ ተናግሯል። ሰልጣኞቹ የተጣለባቸውን ሕዝባዊ አደራ ታማኝነትን በጠበቀ አግባብ ለመወጣት መዘጋጀታቸውንም አረጋግጠዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ ተወካይና የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ መሰንበት መልካሙ እንደገለጹት፤ ሰልጣኝ የሕግ አስከባሪዎች ሰላምን ለማፅናት በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ተገቢው ድጋፍና ክትትል ይደረጋል። የዞኑ ሕዝብ ሰላም ወዳድና የልማት አርበኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሕብረተሰቡ ለፀጥታ አካሉ ተልዕኮ ስኬታማነት እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል። መከላከያ ሰራዊት የ504ኛ ኮር ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ቾምቤ ወርቁ በበኩላቸው፤ ሰራዊቱና የክልሉ የፀጥታ ኃይል የጥፋት ኃይሎችን ተልዕኮ በቅንጅት በማምከን አኩሪ ገድል እየፈፀሙ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ሰላምን የማፅናትና የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ ተግባር እንደ ሁልጊዜው ሁሉ በቀጣይም በሕዝቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
የባንዳ ስራ ላይ የተሰማሩ ኃይሎች ከሀገር ክህደት ተግባራቸው ሊቆጠቡ ይገባል - ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
Nov 3, 2025 127
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ የባንዳ ስራ ላይ የተሰማሩ ኃይሎች ከሀገር ክህደት ተግባራቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ገለጹ። የመከላከያ ሰራዊት የሰሜን ዕዝ ጥቃት የሚዘከረው የተፈጸመው አሳዛኝ ድርጊት መቼም እንዳይደገም ለማስታወስ መሆኑንም የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ገልጸዋል። የመከላለከያ ሰራዊት የሰሜን ዕዝ የተፈጸመበት ጥቃት አምስተኛ ዓመት ዝክረ ሰሜን ዕዝ "እንዳይደገም መቼም አንረሳውም" በሚል መሪ ሀሳብ በቢሾፍቱ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ተከብሯል። ከአምስት ዓመት በፊት ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም የጀግናው መከላከያ ሰራዊት አካል የሰሜን ዕዝ ክህደት እንደተፈፀመበት ይታወቃል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፣ የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰና ሌሎች ከፍተኛ ጄኔራል መኮንኖችና የመከላከያ ሰራዊት አባላት ተገኝተዋል። የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ጥቅምት 24 ቀን የሰሜን ዕዝ ዝክረ ሰማዕታት ቀን ነው። የመከላከያ ሰራዊት የሀገሩን ዳር ዳር ድንበር በማስከበር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆኑንም አውስተዋል። የሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ለትግራይ ክልል ምሽግና አጥር እንደነበር ገልጸው፤ እስከ አሁን ከሰሜን ዕዝ ውጪ በራሱ ዜጎች ጥቃት የደረሰበት አጋጣሚ እንዳልተፈጠረ ተናግረዋል። የመከላከያ ሰራዊት ከራሱ ቀንሶ በትግራይ ብዙ ትምህርት ቤት፣ ጤና ተቋማትና የግብርና ልማት እንዳከናወነ ገልጸው፣ ጥቅምት 24 ቀን የተፈጸመው ድርጊት ግን በኢትዮጵያ ታሪክ ጥቁር ነጥብ ነው ብለዋል። የሰሜን ዕዝ ጥቃት መቼም እንደማይረሳ ገልጸው፤ ቀኑ የሚዘከረው መቼም እንዳይደገም መሆኑን አንስተዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ዕለቱን ሲያስታውሱ፤ መንግሥት በወቅቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተለኮሱ ግጭቶችን ለማብረድ የሚታትርበት እንጂ የጦርነት ዝግጁነት እንዳልነበረው አውስተዋል። መንግሥት ሁልጊዜም ለሰላማዊ መንገድ በሩን ክፍት ማድረጉን ጠቁመው፤ ከትላንት ባለመማር የሚደረግ ፉከራ መቆም አለበት ብለዋል። የቀድሞው ህወሓት ጥቂት አባላት የታጠቁ ኃይሎችን በመደገፍ፣ ሀገር ለማፍረስ ከጎረቤት ሀገር ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ በዲ.ዲ.አር የተሰባሰቡትን በመበተን የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት እየጣሱ መሆኑንም ገልጸዋል። የባንዳ ስራ ላይ የተሰማሩ እነዚህ ህዝቡን የማይወክሉ ኃይሎች ከሀገር ክህደት ተግባራቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባም ተናግረዋል። የመከላከያ ሰራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን በበኩላቸው፤ ከአምስት ዓመት በፊት በሰሜን ዕዝ የሰራዊት አባላት ላይ የተፈፀመው ጥቃት በሀገር ሉዓላዊነት ላይ የተቃጣ ደባ መሆኑን ጠቁመዋል። ዝክረ ሰሜን ዕዝ ወቅቱን በሚመጥን መልኩ እየተከበረ ነው ብለዋል። የተፈጸመው ጥቃት እንዳይደገም መቼም አንረሳውም ያሉት ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው፣ ጥቃቱን ለመመከት ሲሉ መስዋዕትነት የከፈሉ የሰራዊቱ አባላትን ለማስታወስ እና ለተጋድሏቸው ዕውቅና ለመስጠት እንደሚዘከር ገልጸዋል።
ከምክር ቤቱ የመጨረሻ ዓመት የሥራ ዘመን ምን ይጠበቃል?
Nov 3, 2025 105
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ ከ6ኛው ዙር ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመጨረሻ ዓመት የሥራ ዘመን የሚጠበቁ ጉዳዮች ምንድ ናቸው? 6ኛው ዙር የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመን ዘንድሮ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። ምክር ቤቱ በሕገ-መንግስቱ በተሰጠው ሥልጣንና ተግባር መሰረት ሕግ ያወጣል፣አስፈጻሚ ተቋማትን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል። የፓርላማ ዲፕሎማሲ እንዲሁም የህዝብ ውክልና ሥራዎችን ያከናውናል። ምክር ቤቱ ባለፉት አራት ዓመታት ሀገራዊ ለውጡን የበለጠ የሚያሳልጡና የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚመልሱ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን የምክር ቤቱ አባላት ያነሳሉ። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የምክር ቤቱ አባላት በቀሪ የሥራ ጊዜያቸው የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች የበለጠ ውጤታማ እንዲሆኑ በትጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) በተያዘው ዓመት ከሚጠበቁ ጉዳዮች መካከል ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በተመረጡ አጀንዳዎች ላይ የሚያደርገው ውይይት ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሥብራት ለመጠገንና ነባር ችግሮችን በምክክር የመፍታት ባህል ለማዳበር መፍትሄ እንደሚያመጣ እንደታመነበትም ነው ያነሱት። ምክር ቤቱ በቀሪ የሥራ ዘመኑ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባና ችግሮች በምክክር መፍትሄ እንዲያገኙ አበክሮ ይሰራል ብለዋል። የፓርላማ ወዳጅነት ቡድኖች ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰሩ የገለጹት ደግሞ ሌላው የምክር ቤት አባል ሳዲቅ አደም ናቸው። በፓርላማ ዲፕሎማሲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች የሚያስከብሩና የሀገሪቷን የልማት ፍላጎትን የሚያስረዱ ጉዳዮች ላይ በስፋት ይሰራል ብለዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው በተያዘው በጀት ዓመት በኢትዮጵያ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን አስታውሰዋል። የምክር ቤቱ አባላትም በመጨረሻ ዓመት የሥራ ጊዜያቸው እነዚህ ፕሮጀክቶች በተሻለ ፍጥነትና ፈጠራ እውን እንዲሆኑ የተለየ ድጋፍና ክትትል ያደርጋሉ ብለዋል። ለሚቀጥለው ምክር ቤት አስቻይ ሁኔታዎችን ማመቻቸት የ5ኛ ዓመት የምክር ቤት አባላት ድርሻ መሆኑንም አንስተዋል።
የጎንደር ከተማ ነጋዴዎች ለከተማቸው እድገትና ሰላም መስፈን በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እየተወጡ ነው
Nov 2, 2025 239
ጎንደር ፤ ጥቅምት 23/2018 (ኢዜአ):-ለጎንደር ከተማ እድገትና ሰላምን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን በጎንደር ከተማ የንግዱ ማህብረሰብ አባላት ገለጹ፡፡ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችና በአካባቢ ሰላምና ልማት ዙሪያ የከተማው የንግዱ ማህበረሰብ የምክክር መድረክ ዛሬ አካሂደዋል፡፡ ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ አብዱራህማን ሰኢድ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች ዳር እንዲደርሱና ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። በተለይም በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም ለማጽናትና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት መሳተፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ተሾመ ንጉሱ በበኩላቸው እንደ አንድ የንግዱ ማህበረሰብ አባል ህብረተሰቡን የሚያማርሩ ህገወጦችን በማጋለጥ መንግስት ለሰላም መስፈን የሚያደርገውን ጥረት ይበልጥ ለማገዝ እንደሚተጉ አስረድተዋል። የንግዱ ማህበረሰብ የግብር ግዴታውን በመወጣት ለሀገር እድገት የሚያበረክተውን ሚና ማጠናከር እንደሚገባውም ጠቁመዋል። በምንከፍለው ግብር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን በማየታችን ተደስተናል፤ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የድርሻዬን ለማበርከት ዝግጁ ነኝ ያሉት ደግሞ አቶ ጀማል ቃሲም ናቸው፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ጥሩዬ አታክልት እንደገለጹት በከተማው ሰላም መረጋገጡ የንግድ እንቅስቃሴው እንዲነቃቃ አስችሏል። ይህም የንግዱ ማህበረሰብ ሰርቶ በሚያገኘው ልክ የመንግስትን ግብር በታማኝነትና በወቅቱ እንዲከፍል ምቹ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ የንግዱ ማህበሰረብም በሰላም ግንባታ እያበረከተ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡ በምክክር መድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ከስድስት ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የሰላምን አማራጭ ያልተከተሉ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት ዝግጁ መሆን አለባቸው
Nov 2, 2025 252
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 23/2018 (ኢዜአ):- የሰላምን አማራጭ ያልተከተሉ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተናገሩ፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ወቅት እንዳረጋገጡት፤ መንግሥት ወደ ሰላም ከሚመጣ የትኛውም ኃይል ጋር ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን አብሮ ለመስራት ሁል ጊዜም ዝግጁ ነው። በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ የሚስተዋሉ የሰላምና የፀጥታ ችግሮች በዘላቂነት እንዲፈቱ መንግሥት ሰላምን ቀዳሚ አማራጭ አድርጎ እየሠራ መሆኑንም ነው የተናገሩት። መንግስት ሁሌም የሰላም መንገድ ከሚመርጡት ጋር ለመነጋገር ዝግጁ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጠው፤ በአገር ፍላጎት እስከ ተግባባን ድረስ የግል ጉዳይን መተው አስፈላጊ ነው ብለዋል። አሁንም ለሰላም በራችን ክፍት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ካልተደመርንና ካልተጋገዝን የኢትዮጵያን ችግሮች በአጭር ጊዜ ልንፈታ እንደማንችል በመገንዘብ በሰላማዊ መንገድ አብሮ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር)፤ችግሮችን በውይይት መፍታት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ነው ብለዋል። መንግስት ለታጠቁ ኃይሎች ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪዎችን እያቀረበ መሆኑን ገልጸው፤ ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሰላማዊ አማራጭ የመጡ በርካታ ወገኖች መኖራቸውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ አሁን ላይ በፈጣን ዕድገት ላይ እንደምትገኝ ጠቁመው፤ ሀገሪቷ ከምታደርገው የዕድገት ግስጋሴ የሚያስተጓጉላት ነገር ባለመኖሩ ታጣቂዎች ግብ ለሌለው ትግል ጊዜያቸውን ማባከን እንደሌለባቸው አብራርተዋል። መንግስት ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እና ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። በምክክሩ ማንኛውም አካል አለኝ የሚለውን ጥያቄ በማቅረብ በሰላማዊ መንገድ መወያየት እንደሚችል አመልክተዋል። ሌላኛዋ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አስቴር ከፍታው በበኩላቸው፤ አሁን ላይ ቡድኖችንም ሆነ ግለሰቦችን ለትጥቅ ትግል የሚዳርግ ምንም ሁኔታ እንደሌለ ገልጸዋል። የፖለቲካ ልዩነት ያላቸውም ሆኑ የታጠቁ ኃይሎች ለሰላማዊ ውይይት ቅድሚያ በመስጠት ለዘላቂ ሰላም እውን መሆን የበኩላቸውን ድርሻ ማበርከት እንዳለባቸው ተናግረዋል። በትጥቅ የተደገፈ ትግል ሲያደርጉ የነበሩ ኃይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው በመግባት በልዩ ልዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው አገራቸውንና ህዝባቸውን እያገለገሉ ይገኛሉ።
እየተከናወነ ባለው የሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፏችንን ይበልጥ እናጠናክራለን - የባሕርዳር ወጣቶችና ሴቶች
Oct 31, 2025 336
ባሕር ዳር፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፡- በከተማው እየተከናወነ በሚገኘው የሰላም ግንባታና የልማት ተግባራት ላይ ተሳትፏቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የባሕርዳር ከተማ ወጣቶችና ሴቶች ተናገሩ። የከተማው ወጣቶችና ሴቶች በሰላም ማፅናት ዙሪያ ዛሬ በባሕርዳር ከተማ ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊ ትዕግስት አባቡ በሰጠችው አስተያየት፤ መንግስት ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት በማብቃት የሚደነቅ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብላለች። የልማት ስራዎቹ የወጣቶችንና ሴቶችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ጠቅሳ፤ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አንስታለች። ለልማት ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላም ግንባታ ተሳትፎዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል ተናግራለች። ሌላው ተሳታፊ አዲሱ ዳኘው በበኩሉ፤ ከለውጡ ወዲህ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የወጣቶችና ሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ምቹ መደላደል የፈጠሩ ናቸው ብሏል። እየተከናወኑ የሚገኙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሃገሪቱን ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ደረጃ የሚያሸጋገሩ እንደሆኑም ተናግሯል። የልማት ስራዎቹ የተከናወኑት ከሰላም ግንባታ ጎን ለጎን መሆኑን ጠቅሶ፤ የልማት ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲቻል ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጿል። የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ሃላፊ ቶማስ ታምሩ፤ ከለውጡ ወዲሕ በከተማው የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተለይም ከተማዋን ለቱሪስቶችና ነዋሪዎች ምቹ በማድረግ በኩል የኮሪደር ልማት ስራው ለአብነት የሚጠቀስ ዋና ተግባር ነው ብለዋል። ሌሎች የሕዝብ ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ለዚህም የከተማው ወጣቶችና ሴቶች ድጋፍና ትብብር የጎላ መሆኑን አንስተዋል። የተጀመሩ የልማት ስራዎች የወጣቶችንና የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ተጠቃሚነት የበለጠ እንዲያሳድጉ የሰላም መፅናት ወሳኝ በመሆኑ ሴቶችና ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው አፅንኦት ሰጥተዋል። በከተማ አስተዳደሩ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር ዓይን ገላጭ የሆኑ አበረታች የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች፣ ሕፃናትና ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ ሰብለ ዘውዱ ናቸው። ከተማዋ በተፈጥሮ ያላትን ፀጋ በኮሪደር ልማት በማጉላት ከጣና ሃይቅ ጋር ያላት ትስስር ላቅ ወዳለ ደረጃ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ የልማት ተግባራት እንዲሳኩ የበኩላችንን እንወጣለን -ወጣቶች
Oct 31, 2025 264
ደሴ/ወልድያ/ ሰቆጣ፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፡- የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ የልማት ተግባራት ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚወጡ በአማራ ክልል ወጣቶች ገለጹ። "ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ወጣቶች የተሳተፉባቸው የውይይት መድረኮች በደሴ፣ ወልዲያና ሰቆጣ ከተሞች ዛሬ ተካሂደዋል። ከደሴው መድረክ ተሳታፊዎች ውስጥ ወጣት ከድር የሱፍ በሰጠው አስተያየት፤ መንግስት ሰላምን ከማፅናት ጎን ለጎን የሚያካሂዳቸው ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለወጣቶችና ለቀጣዩ ትውልድም ተስፋ የሰጡ ናቸው ብሏል። ፕሮጀክቶቹ የሀገሪቱን እድገት በማፋጠን መሰረታዊ ለወጥ የሚያመጡ መሆናቸውን ጠቅሶ፤ ከሌሎች ወጣቶች ጋር በመተባበር ሰላም በማስጠበቅ ለአካባቢው ልማት ብሎም ለሀገራዊ ፕሮጀክቶች ስኬታማነት የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ሌላዋ የመድረኩ ተሳታፊ ወጣት ቤተልሔም ፈንታው በበኩሏ፣ የማዳበሪያ፣ የጋዝ፣ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያና ሌሎች ፕሮጀክቶች መገንባት ለመጪው ትውልድ ትልቅ ተስፋ የሰነቁ ናቸው ብላለች። በዚህ ሂደት ፕሮጀክቶቹ ተሳክተው የሀገራችንን ብልጽግና ለማረጋገጥ የድርሻችንን ለመወጣት ቁርጠኛ ነን፤ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጅት ሰላማችንን ለማጽናት የጀመርነውን ስራ እናስቀጥላለን ብላለች። የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተወካይና የሕዝብ ግንኙነት ምክትል አማካሪ አቶ አወል አህመድ በበኩላቸው፤ የከተማውን ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ ከወጣቱ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የወል ትርክትን በማስፈን ሕብረብሔራዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ወጣቶች የጀመሩትን የነቃ ተሳትፎ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በተመሳሳይ በወልዲያው መድረክ ከተሳተፉት መካከል ወጣት አቤል አያሌው፤ የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ ልማት ይበልጥ እንዲጠናከር የድርሻችንን ለመወጣት መንቀሳቀስ አለብን ብሏል። ሰላምን በማፅናት የአካባቢውና ሀገራዊ ተስፋ ሰጪ የልማት ተግባራት ከፍጻሜ እንዲደርሱ በጋራ መነሳት አለብን ያለው ደግሞ ወጣት ኃይለማሪያም ስዩም ነው። የወልድያ ከተማ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሀላፊ አቶ መላኩ ዓለሙ፤ ጽንፈኛ ቡድኑ የባዕዳን ተላላኪ በመሆን ታሪክ የማይረሳው አፍራሽ ድርጊት ለመፈፀም ቢሞክርም በፀጥታ ሀይሉ እየመከነበት በመበታተን ላይ መሆኑን አብራርተዋል። ሰላምን በዘላቂት አፅንቶ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት ወጣቶች ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል። በሌላ በኩል በሰቆጣው ውይይት የተሳተፈው ወጣት ጥላሁን አበበ፤ መንግስት ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ እያደረገ ያለው ጥረት እንደግፋለን ብሏል። ሌላው ተሳታፊ ወጣት አስፋው ገብረ መድህን በበኩሉ፤ ለሰላም መስፈን እኛም ከመንግስት ጎን ተሰልፈን የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉ ገልጿል። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ በበኩላቸው፤ በአካባቢ የሰፈነውን ሰላም አስጠብቆ በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ብሎም የፀጥታ አካላት እያደረጉት ያለው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገራችን ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች ላይ አተኩራለች ያሉት አቶ ጌትነት፤ በቀጣናው ያላትን ተሰሚነት ለማጠናከር ወጣቶች ሚናቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል። በከተሞቹ በተካሄደው የውይይት መድረኮች የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ ወጣቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ማህበራዊ
በአዲስ አበባ በ2018 ዓ.ም የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ911 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ይሆናሉ-ኮሚሽኑ
Nov 3, 2025 59
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በ2018 ዓ.ም የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ911 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ገለጸ፡፡ ኮሚሽኑ በበጋ ወራት የሚከናወነውን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት "በጎ ፈቃደኝነት፤ ለማኅበረሰብ ለውጥ" በሚል መሪ ሃሳብ በይፋ አስጀምሯል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አማካሪ አቶ ጥላሁን ሮባ፤ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በነዋሪዎች ሕይወትና በከተማዋ እያመጣ ያለውን ውጤት ማስቀጠል ይገባናል ብለዋል፡፡ ባለፉት ጊዜያት በርካቶች ከበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው ይህን ለማስቀጠልም በጎ ፈቃደኞች በጎ ተግባራቸውን ሊያስቀጥሉ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አስራት ንጉሴ፤ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በርካታ ዜጎች በማኅበራዊና ኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት በአዲስ አበባ ከተማ 42 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር የሚገመቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ ለአብነትም የቤት ግንባታና እድሳት፣ ደም ልገሳ እና አረንጓዴ አሻራን ጠቅሰዋል፡፡ የኮሚሽኑ የበጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ዳይሬክተር ዳዊት ሙሉጌታ በበኩላቸው፤ በዘንድሮው የበጋ ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 9 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ይከናወናል ብለዋል፡፡ ከ911 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ጠቅሰው የቤት ግንባታና እድሳት፣ ማዕድ ማጋራት፣ የጤና አገልግሎት እና የአረንጓዴ ልማት ከሚከናወኑ ሥራዎች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ አረጋውያንና አቅመ ደካሞችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ 1ሺህ 900 ቤቶች እንደሚገነቡም አብራርተዋል። በመርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት በጎ ፈቃደኞች በተከታታይ ዓመታት በመዲናዋ በሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ተግባራት በንቃት ሲሳተፉ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በጎ ፈቃደኞች ማሬ ሙሉጌታ እና ጌታሁን ብርሃኑ ለበጋው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሚከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በድግግሞሽ ከ500 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ በመርኃ ግብሩ ተጠቁሟል።
የካንሰር ሕክምና በቅርበት ማግኘታችን ከእንግልትና ካልተገባ ወጪ ታድጎናል - ታካሚዎች
Nov 3, 2025 95
ሀዋሳ ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦የካንሰር ሕክምና በቅርበት ማግኘታቸው ከእንግልትና ካልተገባ ወጪ እንደታደጋቸው በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የካንሰር ሕክምና ማዕከል ታካሚዎች ገለጹ። መንግስት የሕክምና አገልግሎትን ለዜጎች ተደራሽ ከማድረግ አንጻር የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በተለይ በሀገር ውስጥ እንደ ካንሰር ያሉ የጤና ችግሮችን ዜጎች በአቅራቢያቸው መታከም እንዲችሉ የተለያዩ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። ባለፉት አምስት ዓመታት የካንሰር ሕክምናን በክልሎች ተደራሽ የማድረግ ሥራ በመሰራቱ በአሁኑ ወቅት በማስተማሪያ ሆስፒታሎች ጭምር ሕክምናውን የመስጠት ሥራ ተጀምሯል። ይህም ሕክምናውን ለማግኘት በአዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ እና ጳውሎስ ሆስፒታሎች የነበረውን ወረፋና የሰዎች መጨናነቅ እያቃለለ መሆኑ ነው የተመላከተው። የካንሰር ሕክምና ከተጀመረባቸው መካከል የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የካንሰር ሕክምና ማዕከል አንዱ ሲሆን ታካሚዎችም ሕክምናውን በቅርበት ማግኘታቸው ቀደም ሲል ሲደርስባቸው የነበረውን እንግልትና ወጪ እንዳስቀረላቸው ተናግረዋል። ከሆስፒታሉ ታካሚዎች መካከል ከአርባ ምንጭ በሪፈር ተልከው እንደመጡ የተናገሩት አቶ ችለነው መሰለ፣ በማዕከሉ በተደረገላቸው ምርመራ ችግሩ የደም ካንሰር መሆኑ እንደታወቀላቸው ገልጸዋል። ለካንሰር ሕክምና ወደ አዲስ አበባ ከተማ መምጣት ሳያስፈልግ አገልግሎቱን በቅርበት ማግኘታቸው ከወጪና ከእንግልት ታድጎኛል ሲሉም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በሆስፒታሉ ተገቢ የሕክምና አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአንጀት ካንሰር የታመሙ እናቱን ለማሳከም ከምዕራብ አርሲ ዞን ኮኮሳ ወረዳ እንደመጣ የተናገረው ወጣት ጀማል መሀመድ በበኩሉ በአዲስ አበባ፣ ሻሸመኔ፣ ጎባና ሌሎች ሆስፒታሎች እናቱን ለማሳከም ብዙ መድከሙን ገልጿል። ወደካንሰር ማዕከሉ ከመጡ አንደ ሳምንት እንደሆናቸውና በአሁኑ ወቅት ሕክምናቸውን በጥሩ ሁኔታ እየተከታተሉ መሆናቸውን ገልጿል። የካንሰር ሕክምና ማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ሰለሞን ሁነኛው እንዳሉት ማዕከሉ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ሁለት ዓመት ሆኖታል። እስካሁንም ከ5 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አዋቂና ሕጻናት የካንሰር ሕክምና አገልግሎት መሰጠቱን ጠቁመዋል። ማዕከሉ ከሲዳማ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች እንዲሁም ከኦሮሚያ ባሌ፣ ቦረናና ጉጂ ዞኖች የሚመጡ ሕሙማንን እያገለገለ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በማዕከሉ የህጻናትና የደም ካንሰር ሰብ ስፔሻሊስት ሙሉአለም ንጉሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት የካንሰር ማዕከሉ የህጻናትን ህክምና ክፍል በማቋቋም በሽታ የመለየትና የማከም ሥራ እየሰራ ይገኛል። በቀን እስከ ዘጠኝ ሕጻናት የሕክምና አገልግሎት እንደሚያገኙ ጠቁመው፣ በሕጻናት ላይ በአብዛኛው የደም ካንሰር፣ የጭንቅላት እጢ፣ የአጥንት፣ የኩላሊትና ሌሎች የካንሰር ሕመሞች ይስተዋላሉ ብለዋል። በካንሰር የተያዙ ሕጻናትን በፍጥነት ወደ ሕክምና ማምጣት ከተቻለና ተገቢ ሕክምና ካገኙ የመዳን ዕድል እንደሚኖራቸው አመልክተዋል። በማዕከሉ ለካንሰር ሕመም የጨረር ሕክምና መስጫ መሳሪያ አንድ ብቻ መሆኑና ለ24 ሰዓት ያለሟቋረጥ አገልግሎት እንዲሰጥ በመደረጉ ጫናው ከፍተኛ መሆኑም ተመላክቷል።
በዞኑ የወባ በሽታ ስርጭትን ለመቆጣጠር ህዝቡን በማሳተፍ የመከላከል ተግባር እየተከናወነ ነው
Nov 3, 2025 73
አዶላ፤ ጥቅምት 24/2018 (ኢዜአ) ፡-በጉጂ ዞኑ የወባ በሽታ ስርጭትን ለመቆጣጠር በህዝቡ ተሳትፎ ለወባ ትንኝ መራቢያ ምቹ የሆኑ ውሀ ያቆሩ ቦታዎችን የማዳፈን ፣የኬሚካል ርጭትና የአጎበር ስርጭት እየተካሄደ መሆኑን የጉጂ ዞን ጤና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋዬ በሪሶ ገለፁ፡፡ ስራውን ውጤታማ ለማድረግ በበሽታው መከላከያ ዘዴዎችና ምልክት ላይ በማተኮር ለ14 ሺህ 959 ሰዎች ግንዛቤ መሰጠቱን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም 19 ሺህ 250 ካሬ ሜትር ለወባ መራቢያ አመቺ የሆኑ ውሀ ያቆሮ ቦታዎችን ማዳፈን ፣34 ሺህ 990 ካሬ ሜትር የሚሸፍን የወባ መራቢያ ቦታ ላይ የኬሚካል ርጭት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በዞኑ የጤና ጥበቃ ስራን ውጤታማ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ህዝቡና የባለድርሻ ተሳትፎ እንዲጠናከር ጠይቀዋል፡፡ በዞኑ ሰባ ቦሩ ወረዳ የቀንጢቻ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ኢያሱ ጠዴቻ፣ የክረምቱ መውጣትን ተከትሎ የሚከሰት የወባ በሽታን ለመከላከል በጤና ባለሞያዎች የተሰጣቸውን ግንዛቤ እየተገበሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከአከባቢያቸው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር ለወባ ትንኝ መራቢያ ምቹ የሆኑ ውሀ ያቆሩ ስፍራዎችን ማጽዳታቸውን ገልፀዋል። የዚሁ ወረዳና ቀበሌ ነዋሪ አቶ መልካሙ ነጋሳ የወባ በሽታን ለመከላከል በጤና ባለሙያዎችና በበጎ ፈቃደኞች ያገኙትን ግንዛቤ በመጠቀም የወባ መራቢያ ቦታዎችን ማጽዳታቸውን ተናግረዋል፡፡ በጋራ አካባቢያቸውን የማጽዳትና አጎበርን በአግባቡ መጠቀም እንዲሁም በመንግስት የተደረገው የመድሀኒት ርጭት የወባ በሽታ ስጋታቸውን መቀነሱን ጠቁመዋል፡፡
በክልሉ መደጋገፍን መሠረት ያደረጉ ማህበራዊ ትስስሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 3, 2025 95
ሰመራ፣ጥቅምት 24፣2018(ኢዜአ):- በአፋር ክልል መደጋገፍን መሠረት ያደረጉ ማህበራዊ ትስስሮችን የማጠናከሩ ተግባር በትኩረት እንደሚከናወን የአፋር ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። ቢሮው በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር የቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚዎች የተሻለና የተጠናከረ ድጋፍ የሚያገኙበት ሁኔታ ለማሳደግ የሚያስችል ለሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች፣ ለማህበራዊ ደህንነት ባለሙያዎችና ለማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አስተባባሪዎች ስልጠና መስጠት ጀምሯል። በዕለቱ ተገኝተው መድረኩን የከፈቱት የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ነስሮ ኡዳ እንዳሉት በክልሉ መደጋገፍን መሠረት ያደረጉ ማህበራዊ ትስስሮችን የማጠናከሩ ተግባር በትኩረት ይከናወናል። በሴፍቲኔት መርሃ ግብር እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ አለመሆኑን አንስተው፤ ማህበራዊ ትሰስርን በማጠናከርና በማስተባበር የተለያዩ ባለድርሻዎችን በማሳተፍ የሚደረግላቸው እገዛ ሊጠናከር ይገባል ብለዋል። በየወረዳዎቹ የሚገኙና ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን የጤና መድህን ወጪያቸውን በመሸፈንና አስፈላጊነት ያለውን እገዛ የማድረጉ ተግባርም በስፋት ይሰራል ብለዋል ። በዚህ ረገድ የወረዳ ፅህፈት ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የተዋቀሩትን ኮሚቴዎች በማጠናከር የሚደረገው ድጋፍ እንዲጨምር ሚናቸውን መወጣት እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል። ከፈንቲ ራሱ ዞን አውራ ወረዳ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት የማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ ሙጃሂድ መሐመድ እንዳለው በወረዳው ለሚገኙና ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው አቅመ ደካማ ወገኖች በሴፍቲኔት የታገዘ ድጋፍ ተደርጓል። ይህንን ማህበራዊ ኃላፊነት በመወጣት ረገድ ህብረተሰባችንን በማስተባባበር ቀጣይነት ያላቸው ስራዎችን ማከናወን ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል። የመደጋገፍ ተግባሩ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እፎይታን የሰጠ መሆኑን የገለፀው ደግሞ ከአፋምቦ ወረዳ የመጣው በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት የማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ ኢሴ መሐመድ ናቸው። የተባባበረ ድጋፍን ማጠናከር ላይ ያተኮረው ስልጠናም ለሁለት ቀናት እንደሚቆይም ታውቋል።
ኢኮኖሚ
አዲሱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዓለምን የማስተሳሰር አቅም የሚጨምር ነው- የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ
Nov 3, 2025 31
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ በቢሾፍቱ የሚገነባው አዲሱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዓለምን የማስተሳሰር አቅም የማጠናከር ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ አለው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገለጹ። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ ተጀምሯል። የፎረሙ አካል የሆነ እና በቢሾፍቱ በሚገነባው አዲስ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ግንባታ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል። በውይይቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ የአየር ማረፊያው ግንባታ አጋር የሆነው ዓለም አቀፉ አማካሪ ድርጅት ዳር አል-ሃንዳሳህ እና የግንባታው ከፍተኛ አማካሪ የሆነው ዓለም አቀፍ ተቋም ኬፒኤምጂ ተወካዮች ተገኝተዋል። አየር ማረፊያው ከአውሮፓ ኩባንያዎች ጋር ኢንቨስትመንት እና አጋርነት የሚፈጥር ትልቅ እድል መሆኑ ተገልጿል። የገንዘብ ሚኒስትሩ ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ የሚገነባው አየር ማረፊያ ለውጥ ለማምጣት፣ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እና ዓለም አቀፍ ትስስርን ለማጠናከር ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። የኤርባስ የአፍሪካ ኃላፊ ፌዴሪኮ ቡልቶ ኩባንያው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሻ ገልጸዋል። የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደ ኤምሬትስ እና ኳታር አየር መንገዶች ዓለምን የማስተሳሰር ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርለት ተናግረዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች የአየር ማረፊያ ግንባታውን አስመልክቶ ጠቃሚ ግንዛቤ ማግኘታቸው ተገልጿል። የአውሮፓ ባለሀብቶች በአየር ማረፊያው ግንባታ ለመሳተፍ ፍላጎት ያሳዩበት መድረክ መሆኑንም የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
ተፈጥሮ ተኮር የቱሪዝም ልማት ሥራዎችን ማስፋት የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ ነው
Nov 3, 2025 83
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ተፈጥሮ ተኮር የቱሪዝም ልማት ሥራዎችን ማስፋት የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። ከአስር ዓመታት በፊት የተቋቋመው የዓለም የዱር እንስሳት ፕሮግራም ዓመታዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በጉባኤው ከ30 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የዱር እንስሳት ጥበቃ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ለተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ልዩ ትኩረት በመስጠት አበረታች ውጤቶች አግኝታለች። ቀደም ሲል በታሪክና ባህል ተኮር ቦታዎች ላይ ሰፋፊ የቱሪዝም መዳረሻ ልማት ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን አንስተው፤ ይህ ተግባርም የአካባቢው ማህበረሰብ ኑሮ እንዲሻሻል፣ የስራ እድል እንዲፈጠር እና የውጭ ምንዛሬ እንዲገኝ ማስቻሉን ተናግረዋል። በአሁን ወቅት ከቀድሞዎቹ መዳረሻዎች በተጨማሪ የተፈጥሮ ሀብትና ብሔራዊ ፓርኮችን ለቱሪዝም ልማት የማዋል ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ ብሔራዊ ፓርኮችንና የዱር እንስሳት ልማትን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አንስተው፤ ይህም በኢኮ ቱሪዝም በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑና ለተፈጥሮ ሀብትና ለዱር እንስሳት ጥበቃ ተስማሚ ከባቢ ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣይም ተፈጥሮ ተኮር ቱሪዝምን የበለጠ ለማስፋት በትኩረት እንደምትሰራ ተናግረዋል፡። በተለይም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ የተፈጥሮ ሀብቶች ባሉባቸው ቦታዎች ላይ የቱሪዝም ልማቱን ለማስፋት ስትራቴጂዎች ተቀርጸው እየተተገበሩ መሆኑን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃን ለማጠናከር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያከናወነቻቸውን ተግባራት በጉባኤው ላይ በተሞክሮ ታቀርባለች ብለዋል። የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸውን የስንቅሌ ቆርኬዎችን በሃገር በቀል ዕውቀት ቁጥራቸው እንዲጨምር ማድረግ መቻሉን እና ይህንንም ልምዷን ለሌሎች ሃገራት ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ ተመራማሪ አቶ ፋኑኤል ከበደ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ለምታከናውናቸው ተግባራት ከዓለም አቀፉ የዱር ሕይወት መርሃ ግብር ድጋፍ እየተደረገላት ነው ብለዋል። በመርሃ ግብሩ በኢትዮጵያ በአስር ጥብቅ የተፈጥሮ ቦታዎች ላይ ጥበቃ ማድረግ የሚያስችል የ12 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር የሰባት ዓመታት ፕሮጀክት ይፋ መደረጉንም አንስተዋል። በፕሮጀክቱ ጥበቃ ከሚደረግባቸው ቦታዎች፣ ባቢሌ፣ ጨበራ ጩርጩራ፣ ኦሞና ማጎ ብሄራዊ ፓርኮች እና ጉራ ፈርዳ ጥብቅ ደን ይገኙበታል። የተፈጥሮ ሃብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራውም ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን እየተከናወነ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ የንግድ ግንኙነታቸውን በይበልጥ ለማጠናከር ተስማሙ
Nov 3, 2025 104
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ የንግድ ግንኙነታቸውን በይበልጥ ለማስፋትና ለማጠናከር መስማማታቸው ተገለጹ። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ከፈረንሣይ የውጭ ንግድና ኢኮኖሚ ሚኒስትር ተወካይ ኒኮላስ ፎሪሲየር ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም፤ የሁለትዮሽ የኢኮኖሚ ትብብርን በይበልጥ ማሳደግ እና በኢትዮጵያ ተጨማሪ የፈረንሳይ ኢንቨስትመንትን ማበረታታት በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ መክረዋል። በዚህም መሠረት ሀገራቱ በዘላቂና ሁሉን አቀፍ ዕድገት ላይ የነበራቸውን ትብብር ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆናቸው ተገልጿል። ለአብነትም፤ በኢንዱስትሪ ልማት፣ ታዳሽ ኃይል፣ መሠረተ-ልማት፣ የግብርና ማቀነባበሪያ፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ጨምሮ በሌሎች ዘርፎች በትብብር የሚከናወኑ ተግባራት መኖራቸው ተጠቁሟል። አቶ አሕመድ በውይይቱ ወቅት ፈረንሳይ ለኢትዮጵያ የልማት ተነሳሽነት ላደረገችውና እያደረገች ላለው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አመሥግነዋል። ኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ዘርፉን በይበልጥ ለማሻሻል እየሠራች መሆኗን ጠቁመው፤ ለአብነትም ፖሊሲን ጨምሮ ተቋማዊ ሪፎርሞች ማድረጓን አስታውቀዋል። ይህም በዘርፉ በይበልጥ ቀጣይነት ያለው ዓለም አቀፍ ተሳትፎን ከማሳደግ ባለፈ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ለማግኘት ማስቻሉን ነው ያስረዱት። የኢትዮጵያን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት የኢኮኖሚ ትስስሩን ማስፋትና ማጠናከር እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል። ኒኮላስ ፎሪሲየር በበኩላቸው የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማሻሻያ አድንቀው፤ ፈረንሳይ በቀጣይም የንግድ ትስስሩን ለማስፋት፣ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ብሎም የኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። በፈረንጆቹ ግንቦት 2026 የፈረንሣይ ልዑክ ወደ ኢትዮጵያ በሚያደርገው ይፋዊ ጉብኝት ሁለቱም ወገኖች ውይይቱን ለመቀጠል መስማማታቸው ተመላክቷል።
ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብራቸውን ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Nov 3, 2025 98
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ ትብብራቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ መካሄድ ጀምሯል። በመክፈቻው ስነ ስርዓት ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል እያከናወነቻቸው ያሉ ስራዎችንም አድንቀዋል። ኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ምቹነትን ለማሻሻልና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብን አላማ በማድረግ እያደረገቻቸው ያሉ የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ ምክክሮች መልካም የሚባሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በኢንቨስትመንት ፎረሙ ላይ ኢትዮጵያ በግብርና ንግድ፣ የታዳሽ ኃይል፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና መሰረተ ልማትን ጨምሮ ቁልፍ የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት እድሎች ቀርበዋል። በፎረሙ የአውሮፓ ህብረት የ"ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" ማዕቀፍ ያለው ጠቀሜታም ተነስቷል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ ሰላምና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብርና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ማዕቀፉ የሁለቱ ወገኖች ትብብር ለማጠናከርና ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽንና ዘላቂ እድገት የሚውል የአውሮፓን ኢንቨስትመንት ለማሰባሰብ እንደሚያግዝ ተመላክቷል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የዲጂታል መታወቂያ በተለያዩ አካባቢዎች ለማዳረስ የሚያስችል የአገልግሎት ማዕከላትን የማስፋት ስራ እየተከናወነ ነው
Nov 2, 2025 218
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 23/2018 (ኢዜአ):-የዲጂታል መታወቂያ አገልግሎትን በተለያዩ አካባቢዎች ለማዳረስ የሚያስችል የአገልግሎት ማዕከላት ማስፋት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምዝገባ አስተባባሪ ደጀኔ ገብሬ ገለጹ፡፡ እስካሁን ከ27 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝግበዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምዝገባ አስተባባሪ ደጀኔ ገብሬ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ለሁሉም ነዋሪዎች ዲጂታል መታወቂያን በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ ሰፋፊ ተግባራት እየተከናወኑ ነው። የምዝገባ አገልግሎቱን በተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች ለማዳረስ ከአጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የአገልግሎት ማዕከላት በማስፋት ምዝገባ እያካሄደ ነው። በተጨማሪም አገልግሎቱ ወደ ሩቅ አካባቢዎች እንዲደርስ በተንቀሳቃሽ የምዝገባ ጣቢያዎች (Mobile Registration Units) አማካኝነት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት ከአምስት ሺህ በላይ የመመዝገቢያ ማሽኖች አገልግሎት ላይ ናቸው ያሉት አስተባባሪው፤ ከ27 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝግበዋል ብለዋል። እስከ በጀት ዓመቱ አጋማሽ ድረስ የመመዝገቢያ ማሽኖቹን ቁጥር ወደ 10 ሺህ በማሳደግ ተደራሽነትን ለማስፋት መታቀዱን ገልጸዋል። በአጠቃላይ በዓመቱ ውስጥ 60 ሚሊዮን ዜጎችን ለመመዝገብ ዕቅድ የተያዘ ሲሆን፤ ይህንኑ ለማሳካት ጠንካራ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስተባባሪው አስረድተዋል። የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የዲጂታል ኢኮኖሚውን በማሳደግ፣ የገንዘብ ማጭበርበርን በመቀነስ እንዲሁም የመንግሥትና የግል አገልግሎቶችን ይበልጥ ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተገልጿል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችለንን የዲጂታል ክህሎትለማወቅ እየተጋን ነው
Nov 1, 2025 193
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 22/2018(ኢዜአ)፡-በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችለንን የዲጂታል ክህሎት ለማወቅ እየተጋን ነው ሲሉ በመዲናዋ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ። የአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ የስልጠና መርኃ ግብር የዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ ፕሮጀክት ነው። ይህም የቴክኖሎጂ እውቀት በማበልጸግ በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን ብቃት እንዳስጨበጣቸው መርኃ ግብሩን ተከታትለው የጨረሱ ሰልጣኞች በተደጋጋሚ ገልጸውታል። መርኃ ግብሩ ዜጎች በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በዳታ ሳይንስ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግና በዌብ ፕሮግራሚንግ ወሳኝ እውቀትንና ክህሎትን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዚህ ሳምንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተካሄደው አምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ጋር በተያያዘ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም አሁን ላይ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና መውሰድ መቻላቸውን አስታውቀዋል። መንግሥት ያመቻቸውን እድል በመጠቀም ስልጠናውን እየወሰዱ ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል ተማሪዎች ተጠቃሽ ናቸው። ተማሪዎቹ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ነባራዊ ሁኔታ በቂ የሆነ የዲጂታል እውቀትና ክህሎት የሚጠይቅ ነው ብለዋል። በኮከበ ፅባህ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ አቤኔዘር ዘገዬወርቅ ስልጠናው ከመደበኛ ትምህርታችን ጎን ለጎን የዲጂታል አቅማችንን እንድናጎለብት አስችሎናል ብሏል። ከቀረቡት መርኃ ግብሮች መካከል በዌብ ፕሮግራሚንግ እና ዳታ ሳይንስ ስልጠና መውሰዱን ገልጿል። ያገኘው ስልጠና ጊዜው የሚጠይቀውን የዲጂታል እውቀት እንዲገበይ እንዳደረገው በመግለጽ ቀሪዎቹን የኮደርስ የስልጠና መርኃ ግብሮች በቀጣይ ለመውሰድ መዘጋጀቱን ጠቅሷል። በስልጠናው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተሻለ ክህሎት ማግኘቷን የገለጸችው ደግሞ የብርሃን ጉዞ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ህይወት ተስፋሁን ናት። አርቴፌሻል ኢንተለጀንስ በተመለከተ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራት ትፈልግ እንደነበረ በመጠቆም መርኃ ግብሩ ፍላጎቷን እውን እንድታደርግ እንዳስቻላት ገልጻለች። በኮከበ ጽባህ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሀናን ኢብራሂም በበኩሏ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ ስልጠና መውሰዷ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በቀላሉ ለመረዳት እንዳስቻላት ጠቅሳለች። የብርሃን ጉዞ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ኪሩቤል ሀብተስላሴ ዲጂታል ቴክኖለጂውን በሚገባ ለመረዳት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ጠቅሶ ስልጠናው ክህሎቱን ለማጎልበት እንዳስቻለው ተናግሯል። የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ ቢሮው ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ተማሪዎች የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ከ2017 ጀምሮ ከ40 ሺህ በላይ ተማሪዎች የኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸውን አስታውቀዋል። ቢሮው የዲጂታል እውቀትና ክህሎት የተላበሰ ትውልድ ለመፍጠር የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ስልጠናውን የተከታተሉ ተማሪዎች ወጣቶች ከመደበኛ ትምህርት ጎን ለጎን የኮደርስ ስልጠናን በመውሰድ ያላቸውን የዲጂታል ህሎት እንዲያጎለብቱ ጥሪ አቅርበዋል።
የወጣቶችን የፈጠራ ሃሳብ ወደተግባር የሚቀይር የፋይናንስ አቅርቦት አሰራር መዘርጋቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማፋጠን ጉልህ ጠቀሜታ አለው
Oct 31, 2025 186
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-የወጣቶችን የፈጠራ ሃሳብ ወደተግባር የሚቀይር የፋይናንስ አቅርቦት አሰራር መዘርጋቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማፋጠን ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተገለጸ። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማሳለጥ ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል የሚፈጠርለትን የሥራ ዕድል ከክህሎቱ የሚያገናኝ ምቹ አሰራር ሥርዓት ምኅዳር መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑ እሙን ነው። ይህም ወጣቶች ክህሎታቸውን በመጠቀም በሚፈጠርላቸው የሥራ ዕድል ለሀገር ዕድገትና ከፍታ ችግር ፈቺ ስኬቶችን እንዲያስመዘግቡ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፤ ከግማሽ በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ወጣት መሆኑ ለሀገር ዕድገትና ብልጽግና ከፍተኛ አቅም እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የልማት አቅም የሆነውን ወጣት ኃይል የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ስኬት እየተመዘገበ ቢሆንም ቀጣይነት ያላቸው ስራዎችን ማከናወን እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። የወጣቶችን በክህሎት የታገዘ ሥራ ፈጣሪነት አቅም ለማሳደግ የሚከናወኑ ተግባራትም በሁሉም መመዘኛ መሰናክሎችን ማለፍ እንደሚጠይቅ አስረድተዋል። በዚህም የለውጡ መንግስት ወጣቶች በተለያዩ መስኮች በሚፈጠርላቸው የሥራ ዕድል ለሀገር ልማትና ዕድገት የድርሻቸውን የሚወጡበትን ምቹ ምኅዳር መፍጠር እንደቻለ ገልጸዋል። በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የዜጎችን የሥራ ዕድል አማራጭ ተጠቃሚነትን ለማስፋትም የተቀረጹ የአሰራርና የሕግ ማዕቀፎች ውጤት እያስመዘገቡ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ወጣቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን ወደተግባር ለመቀየር የሚያጋጥማቸውን የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍም የወጣቶች የኢንቨስትመንት ባንክ ለማቋቋም ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የወጣቶች የኢንቨስትመንት ባንክም በኢትዮጵያ የገበያ ሥርዓት የተመዘገቡ ኢንተርፕርነሮች የሚያቀርቡት የሥራ አዋጭነት ተጠንቶ ያለምንም ማስያዣ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት መሆኑን አስታውቀዋል። የወጣቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ዕድገት እያስመዘገበ ነው ያሉት ሚኒስትሯ በተያዘው በጀት ዓመትም ለአምስት ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የምጣኔ ሃብት ምሁሩ ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር)፤ መንግስት ዜጎች የሥራ ዕድል የሚያገኙበትን ምቹ የአሰራር ምኅዳር የመፍጠር ኃላፊነት አለበት ብለዋል። በዚህም ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ክህሎታቸውን ወደ ተግባር የሚቀይሩበትን የፋይናንስ አቅርቦት ለማሻሻል የተፈጠሩ የአሰራር ሥርዓቶች የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋት ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖራቸው ገልጸዋል። ይህም ወጣቶች የፈጠራ ሀሳባቸውን ወደ ተግባር በመቀየር ተጨማሪ የሥራ ዕድል አቅሞችን በማስፋት በሀገራዊ የኢኮኖሚ እድገት ላይ አዎንታዊ ሚና ማበርከት እንደሚያስችል አስረድተዋል። በቅርቡም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ትብብር የወጣቶች የኢንቨስትመንት ባንክ ማቋቋም የሚያስችል ሥምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።
በክልሉ የግብርና ምርምር ማዕከላት ግብርናን በማዘመን ለዘርፉ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ አድርገዋል - ቢሮው
Oct 30, 2025 192
ወራቤ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ምርምር ማዕከላት ግብርናን በማዘመን ለዘርፉ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል ለስርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም በዘር ብዜት፣ በምርምርና በቴክኖሎጂ ሽግግር ባከናወናቸው ተግባራት ላይ የመስክ ምልከታ ተካሂዷል። የቢሮው ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ ዓለምይርጋ ወልደስላሴ በዚህ ወቅት እንዳሉት በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ምርምር ማዕከላት ተጨማሪ አቅም እየሆኑን ነው። በግብርና ዘርፍ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በራስ አቅም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ከተረጂነት ለመወጣት እየተደረገ ባለው ጥረት ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል። በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ ዐሻራና በሌሎች የግብርና ሥራዎችም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት በማሳደግ በኩል ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ነው የጠቆሙት። ባለፈው ዓመት በክልሉ በበልግ፣ በመኸርና በበጋ መስኖ ልማት 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር ማሳ በማልማት 142 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ገልጸዋል። ለዚህም የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርጥ ዘር ብዜት፣ የተሻሻሉና በምርምር የተደገፉ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በማሸጋገር ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አስታውሰዋል። በዚህ ዓመትም 159 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ግብ ተጥሎ ወደ ተግባር መገባቱን ነው ምክትል ቢሮ ኃላፊው የተናገሩት። የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ያዕቆብ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ የግብርና ልማት ሥራውን የሚያግዙ ተግባራት በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የሀገራዊና ክልላዊ ኢንሼቲቮች ትግበራን በምርምርና በቴክኖሎጂ እያገዘ እንደሚገኝም ነው የገለጹት። የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ቀድራላ ዋበላ(ዶ/ር) እንዳሉት ማዕከሉ ግብርናን ማዘመን የሚያስችል የምርምር፣ የዘር ብዜትና ቴክኖሎጂን የማስተዋወቅ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የአካባቢን ስነ ምህዳር መሰረት በማድረግ የዘር ብዜት፣ የሰብል ጥበቃና እንስሳት ዝርያ ማሻሻልን ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመስክ ምልከታው የክልሉ ግብርና ቢሮ፣ የምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ አመራሮችና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።
ስፖርት
በፕሪሚየር ሊጉ ሸገር ከተማ እና ሃዋሳ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል
Nov 3, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአራተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ተካሄደዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን በያሬድ መኮንን ግብ 1 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎ ሸገር ከተማ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን ሲያስመዘግብ ቅዱስ ጊዮርጊስ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ሽንፈቱን አስተናግዷል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታን 3 ለ 1 ረቷል። ጌታነህ ከበደ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ያሬድ ብሩክ ቀሪዋን ጎል ለሃዋሳ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሱሌይማን ሃሚድ ለመቀሌ 70 እንደርታ ብቸኛዋን ጎል ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ሃዋሳ ከተማ በሊጉ ሶስተኛ ድሉን ሲያስመዘግብ በተቃራኒው መቀሌ 70 እንደርታ ሶስተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል። ዛሬ አስቀድሞ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸንፏል።
የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ድሉን አስመዘገበ
Nov 3, 2025 65
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአራተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን የመጀመሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ዩጋንዳዊው አለን ካይዋ እና የሀዲያ ሆሳዕናው ተከላካይ ዳግም ንጉሴ በራሱ ግብ ላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ተመስገን ብርሃኑ ለሀዲያ ሆሳዕና ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ የሊጉ የወቅቱ የዋንጫ ባለቤት ኢትዮጵያ መድን በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። መድን ሁለት ተስተካካይ ጨዋታ ይቀረዋል። ሀዲያ ሆሳዕና በሊጉ ሁለተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል። ቡድኑ በውድድር ዓመቱ እስከ አሁን ድል ማስመዝገብ አልቻለም።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአራተኛ ሳምንት ተጠባቂ ጨዋታዎች
Nov 3, 2025 92
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አራተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከቀኑ 7 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ሀድያ ሆሳዕና ከኢትዮጵያ መድን ይጫወታሉ። ሀድያ ሆሳዕና በሁለት ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በአንድ ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። ኢትዮጵያን መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ከግብጹ ፒራሚድስ ጋር በነበረው ጨዋታ ምክንያት የሁለተኛ እና ሶስተኛ ሳምንት ጨዋታዎቹ መራዘማቸው ይታወቃል። ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ የመጀመሪያ ሶስት ነጥብ ለማግኘት ይጫወታሉ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሸገር ከተማ ከቀኑ 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በሊጉ ካደረጋቸው ሁለት ጨዋታዎች ስድስት ነጥብ ያገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በሊጉ ካካሄዳቸው ሁለት ጨዋታዎች አንድ ነጥብ በማግኘት አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው 17ኛ ደረጃን ይዟል። በዚሁ ዕለት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም መቀሌ 70 እንደርታ ከሃዋሳ ከተማ ጋር ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በሊጉ ባደረጋቸው ሶስት ጨዋታዎች አንድ ነጥብ ብቻ ያገኘው መቀሌ 70 እንደርታ 18ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ ከሶስት ጨዋታ ስድስት ነጥብ በመሰብሰብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። መቀሌ 70 እንደርታ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን ለማግኘት ይጫወታል። ሃዋሳ ከተማ ካሸነፈ በሊጉ ሶስተኛ ድሉን ያስመዘግባል።
ማንችስተር ሲቲ ደረጃውን ወደ ሁለተኛ ከፍ ያደረገበትን ወሳኝ ድል አስመዘገበ
Nov 2, 2025 149
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 23/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ10ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንችስተር ሲቲ ቦርንማውዝን 3 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በኢትሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አርሊንግ ሃላንድ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ኒኮ ኦራይሊ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ግቦች ወደ 11 ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት መሪነቱን አጠናክሯል። ታይለር አዳምስ ለቦርንማውዝ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ማንችስተር ሲቲ በሊጉ ስድስተኛ ድሉን በማስመዝገብ ደረጃውን ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ቦርንማውዝ በ18 ነጥብ ከሶስተኛ ደረጃ ወደ አራተኛ ዝቅ ብሏል። ቀን ላይ በተደረገ ጨዋታ ዌስትሃም ዩናይትድ ኒውካስትል ዩናይትድን 3 ለ 1 በመርታት ከሶስት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ ድል ተመልሷል። በሊጉም ሁለተኛ ድሉን አግኝቷል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 10ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ነገ ሰንደርላንድ ከኤቨርተን በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል። ሊጉን አርሰናል በ25 ነጥብ እየመራ ይገኛል።
አካባቢ ጥበቃ
በመካከለኛው፣ምስራቅ እና የደቡባዊ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ እየጨመረ ይሄዳል
Nov 3, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 24/2018(ኢዜአ)፦በመካከለኛው፣ምስራቅ እና የደቡባዊ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ እንደሚሄድ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በመካከለኛው፣ምስራቅ እና የደቡባዊ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች የአየሩ ሁኔታ እንደሚቀያየር አስታውቋል። በደብረ ብርሃን፣አርሲ ሮቤ፣አዳባ፣ደሴ፣ባሌ ሮቤ፣አዲስ አበባ፣አደሌ፣አምባ ማሪያም፣ ኮምቦልቻ፣ አንኮበር በአብዛኛው ቀናቶች ላይ ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየስ በታች እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል። የበጋ ወቅት ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑት የደቡብ፣ደቡብ ምዕራብና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚቀጥሉት አስር ቀናት ዝናብ ያገኛሉ ተብሏል። በሌላ በኩል አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የበጋው ደረቅ፣ጸሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ተጠናክሮ ይቀጥላል። በመካከለኛው፣የምስራቅ እና ደቡብ ደጋማ ቦታዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ እንደሚሄድ የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል። ደቡብ ምዕራብ፣ ደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራቸዋል። የመኽር ሰብል አብቃይ በሆኑት የደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች በወሩ ያለው እርጥበት ዘግይተው ለተዘሩት፣ የእድገት ጊዜያቸውን ላልጨረሱ ሰብሎች፣ለቋሚ ተክሎችና ፍራፍሬዎች የውሃ ፍላጎት ለማሟላት ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ገልጿል። ያለው እርጥበት ለእንስሳት መኖም አዎንታዊ አበርክቶ እንዳለው ጠቁሟል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበጋ እርጥበት ተጠቃሚ ተፋሰሶች ላይ የተሻለ የገጸ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው የሚጠበቅ ሲሆን የተቀሩት ተፋሰሶች ዝቅተኛ እርጥበት እንደሚኖራቸው ትንበያው ያሳያል ብሏል። አብዛኛው የባሮ አኮቦ፣ኦሞ ጊቤ፣ገናሌ ዳዋ፣ኦጋዴን፣ በመካከለኛው እና በታችኛው ስምጥ ሸለቆ፣ዋቤ ሸበሌ የተሻለ የገጸ ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው ጠቁሟል። አብዛኛው አፋር ደናክል፣አዋሽ፣ተከዜ፣መረብ ጋሽ እንዲሁም አይሻ ተፋሰሶች ላይ ደረቅ የአየር ሁኔታ ጠባይ ተጽዕኖ ስር እንደሚወድቁ የአየር ትንበያ ያሳያል ብሏል።
የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ቃል ኪዳን እና የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጉዞ
Oct 31, 2025 273
ብዝኃ ህይወት ሁሉንም ሥነ-ሕይወታዊ ኃብቶች፣ እፅዋት፣ እንስሳትና ደቂቅ አካላት እንዲሁም በውስጣቸው የያዟቸው ዘረ-መሎችና እነዚህ የሚፈጥሯቸውን ውህዶች የሚያካትት ነው። የሁሉም ስርዓተ ምህዳር እና የሰው ልጆች የመኖር መሰረት ነው ብዝሃ ህይወት። እንደ አንዳንድ ጥናቶች ከሆነ በዓለማችን ካሉ ህይወት ካላቸው 8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዝርያዎች መካከል 80 በመቶዎቹ ገና ያልተገኙ ናቸው። የዓለም ብዝሃ ህይወት ቁልፍ ጠቀሜታዎች አሉት። የምግብ ምርታማነት፣ ንጹህ ውሃ እና አየር፣ ለርክበብናኝ (ፖሊኔሽን) እና አየር ንብረትን መቆጣጠርን ጨምሮ በርካታ ጠቃሜታዎች እንዳሉት የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ብዝሃ ህይወት ከ44 ትሪዮን ዶላር በላይ ወይም የዓለምን ዓመታዊ 50 በመቶ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) ይሸፍናል። የዓለም የብዝሃ ህይወት እና የስነ ምህዳር አገልግሎቶች የበይነ መንግስታት የሳይንስ ፖሊሲ መድረክ ((IPBES) በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ በሰው የተለያዩ ተግባራት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የመሬት አጠቃቀም ምክንያት አንድ ሚሊዮን ገደማ ህይወት ያላቸው ዝርያዎች ሊጠፉ እንደሚችሉ ስጋቱን አስቀምጧል። በዚህ የዓለም ቀውስ ውስጥ አፍሪካ የብዝሃ ህይወት እምቅ ሀብቶች ያላት አህጉር ሆና ተገኝታለች። የብዝሃ ህይወቱ በርካታ እና ጫና መቋቋም የሚችሉ የአይበገሬነት አቅም ያላቸው ናቸው። የዓለም አንድ አምስተኛ እጽዋት፣ አጥቢ እንስሳት እና አዕዋፋት የሚገኙት በአፍሪካ ነው። ከ50 ሺህ በላይ የእጽዋት ዝርያዎች፣ 1 ሺህ 100 አጥቢ እንስሳት፣ 2 ሺህ 500 የአዕዋፋት እና ከ3000 በላይ የአሳ ዝርያዎች ይገኛሉ። የዓለማችን ሁለተኛው ጥብቅ ደን የኮንጎ ጥቅጥቅ ደን፣ የቦትስዋና ኦካንጋቮ ዴልታ፣ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ስፍራዎች እና የማዳጋስካር ልዩ ስነ ምህዳሮችና ዝርያዎች ከአፍሪካ ዋነኛ ብዝሃ ህይወቶች መካከል ይጠቀሳሉ። የአፍሪካ ብዝሃ የኔዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ ከማሻሻል ባለፈ የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት በዘላቂነት ማስቀጠል የሚችል አቅም ያለው ነው። ይሁንና የአፍሪካ ብዝሃ ህይወቶች ለተለያዩ ፈተናዎች የተጋለጡ ናቸው። አህጉሪቷ በየዓመቱ 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር ገደማ ደን እንደምታጣ መረጃዎች ያሳያሉ። እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ህዝብ ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቀው የአፍሪካ ህዝብ፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ህገ ወጥ አደን ፣ ዘላቂነት የጎደለው የመሬት አጠቃቀም እና ብክለት የአህጉሪቷን ብዝሃ ህይወት ስርዓት እየጎዱ ይገኛሉ። የአፍሪካ ጥብቅ ስፍራዎች ለማስተዳደር በዓመት ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያስፈልግ ቢሆንም አንዳንድ ሀገራት በቂ ኢንቨስመንት እየመደቡ አይገኝም። አፍሪካ የሶስትዮሽ ተፈጥሯዊ ቀውሶችን እያስተናጋደች ትገኛለች ማለት ይችላል። የብዝሃ ህይወት መመናመን፣ ብክለት እና የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ተግዳሮቶች ናቸው። የአስተዳደር ስርዓት አለመጠናከር፣ የተገደበ የፋይናንስ አቅርቦት እና የአካባቢ ማህበረሰብ መሪዎች በውሳኔ መስጠት ውስጥ አለመሳተፋቸው በዋናነት የሚጠቀሱ ፈተናዎች እንደሆኑም ይነገራል። የአፍሪካ ሀገራት የብዝሃ ህይወት ችግሮችን ለመፍታት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛል። ከነዚህም አንዷ ኢትዮጵያ ናት። ኢትዮጵያም ከፍተኛ የብዝኃ ሕይወት ኃብት ካላቸው አገራት መካከል አንዷ ናት። አሁን ላይ አገሪቱ ከ6 ሺህ በላይ የእፅዋት ኃብቶች ያላት ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ 600 ወይም 10 በመቶ የሚሆኑት በአገሪቱ ብቻ የሚገኙ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢንስቲትዩት መረጃ ያመለክታል። ጎን ለጎንም የወፍ ዝርያዎችን ጨምሮ በየብስና በውኃ አካላት ውስጥ የሚኖሩ የተለያዩ ዓይነት ዝርያ ያላቸው በርካታ እንስሳት በኢትዮጵያ ይገኛሉ። ይሁንና የየብስና የውኃማ አካላት አካባቢ መለወጥ ለእነዚህ ብዝኃ ሕይወት ኃብቶች ሥጋት እየሆነ መምጣቱን ነው ኢንስቲትዩቱ የገለጸው። በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለትና ዘለቄታዊ ያልሆነ የተፈጥሮ ኃብት አጠቃቀም ለብዝኃ ሕይወት ኃብቶች መመናመን ምክንያቶች ናቸው። የሕዝብ ቁጥር መጨመርን ተከትሎ ደን ወደ እርሻ መሬትነት መቀየር እንዲሁም መጤ ወራሪ አረሞች ነባር አገር በቀል ዝርያዎች የሚበቅሉበትን ሥፍራ መያዝም ሌላኛው ምክንያት ነው። ይህንንም ተከትሎ ወይራ፣ ዝግባ፣ ቀረሮ፣ ዋንዛ፣ ጥቁር እንጨትና ኮሶ እየተመናመኑ ካሉ የእፅዋት ብዝኃ ሕይወት ዝርያዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ዝርያዎቹ አንዴ ከጠፉ መልሰው የማይገኙ በመሆናቸው ኢንስቲትዩቱ ዝርያዎቹን የማራባትና የማብዛት ሥራ በልዩ ትኩረት እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። ከእነዚህም በተጨማሪ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውና በኢትዮጵያ ብቻ ያሉ የእፅዋትና እንስሳት ብዝኃ ሕይወት ዝርያዎችን የመጠበቅ ሥራ እየተከናወነ ነው። በዚህም የቀረሮ የእጽዋት ዝርያ የማብዛት ሥራ እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች የተመናመኑ የዳልጋ ከብቶች ወደ ነበሩበት የመመለስ ሥራም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። በተመሳሳይ "የሸኮ ዳልጋ ከብት" እየተባለ የሚጠራውን ዝርያ የማብዛት እንዲሁም በጣና ኃይቅ የዓሳ ዝርያዎች ላይ ያለውን መመናመን ለመቀልበስም የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ነው ኢኒስቲትዩቱ ያስታወቀው። ጥብቅ አካባቢዎችን የማስፋት፣ የእፅዋት አፀድ ጥበቃ፣ የዘረመልና የማኅበረሰብ የዘር ባንኮችን በየአካባቢው የማስፋት ተግባርም እየተሰራ መሆኑን አመልክቷል። የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብርም የብዝኃ ሕይወትን ከመጠበቅና ከማስቀጠል አኳያ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ያሏትን የብዝኃ ሕይወት ሃብቶች የመጠበቅ ተልዕኮ የተሰጠው የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩትም ኃብቶቹን የማንበር (የመጠበቅ)፣ ዘለቄታዊ አጠቃቀምና ፍትሃዊ የጥቅም ተጋሪነት ላይ እየሰራ ይገኛል። በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎች እና ቀጣይ እርምጃዎች የሚመክር ጉባኤ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ከጥቅምት 23 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ቃል ነው። ጉባኤው ለአፍሪካ ብዝሃ ህይወት መመናመን፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ብክለት የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ መስጠት የሚያስችል መድረክ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። የአፍሪካ ቀዳሚ የብዝሃ ህይወት አጀንዳዎች ምክክር ይደረግባቸዋል። አህጉር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ትስስርን ማጠናከር እና ለብዝሃ ህይወት ክብካቤ የፋይናንስ ሀብትን በተቀናጀ ሁኔታ ማሰባሰብ ሌሎች የጉባኤው አጀንዳዎች ናቸው። ኢትዮጵያ እና የጉባኤው አዘጋጅ ቦትስዋን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት በብዝሃ ህይወት ጥበቃ እያከናወኗቸው ያሉ ስራዎችን አስመልክቶ ልምዳቸውን ያጋራሉ። እ.አ.አ በ2026 በአርሜኒያ በሚካሄደው 17ኛው የዓለም የብዝሃ ህይወት ጉባኤ (ኮፕ 17) ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች የአፍሪካን ድምጽ በጋራ ማሰማት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ይደረጋል። ጉባኤው አንድ ብዝሃ ህይወት የልማት አቅም ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ብልጽግና አረጋጋጭ ሞተር መሆኑ ግልጽ መልዕክት የሚተላለፍበት መድረክ ነው። ፍላጎቶች ተጨባጭ እና መሬት ወደወረዱ መፍትሄዎች ማውረጃ አማራጭ ሆኖም ያገለግላል። በአርሜኒያ ለሚገሄደው ዓለም አቀፍ ጉባኤ አፍሪካ ፍትሃዊ የፋይናንስ አቅርቦት እንድታገኝ፣ ሁሉን አቀፍ የብዝሃ ህይወት አስተዳደር እንዲረጋገጥ እና ለፍትሃዊ የጥቅም ተጋሪነት ድምጿን ለማሰማት ስንቅ ለሚሆን የሚያስችል አህጉራዊ መድረክ ጭምር ነው ማለት ይቻላል። በአፍሪካ ያለውን የብዝሃ ህይወት አቅም በውጤታማ የአስተዳደር ስርዓት፣ አካታች የማህበረሰብ ተሳትፎ እና ዓለም አቀፍ ትብብር አማካኝነት ወደ ዘላቂ እድገት ምንጭነት ማሸጋገር እንደሚቻል ጥርጥር የለውም። የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ስራ ለዓለም የብዝሃ ህይወት ግቦች መሳካት ትልቅ አበርክቶ ይኖረዋል። በብዝሃ ህይወት ላይ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ለአፍሪካ መጻኢ ጊዜ መሰረት እንደመጣል ይቆጠራል።
የአኙዋ ባዮስፌር በዩኔስኮ መመዝገቡ ኢትዮጵያ በብዝሃ ሕይወት ጥበቃና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂዎች ስኬት እያስመዘገበች ለመሆኑ ሁነኛ ማሳያ ነው
Oct 31, 2025 239
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-የአኙዋ ባዮስፌር በዩኔስኮ በሰውና ባዮስፌር (ማፕ) መርሃ ግብር መመዝገቡ ኢትዮጵያ በብዝሃ ሕይወት ጥበቃና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂዎች ስኬት እያስመዘገበች ለመሆኑ ሁነኛ ማሳያ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። ባዮስፌር ሪዘርቭ ሰውና ተፈጥሮን አስማምቶ ማኖር የሚያስችል የጥበቃ ስልት ነው። በጋምቤላ ክልል የሚገኘው የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ለኢትዮጵያ ስድስተኛው የባዮስፌር ሪዘርቭ በመሆን በዩኔስኮ ተመዝግቧል። ባዮስፌሩ ስድስት የተለያዩ ሥነ-ምህዳሮችን ያካተተ ሲሆን እርጥብ የአፍሮ-ሞንታኔ ደኖች፣ የሽግግር የዝናብ ደኖች፣ የወንዝ ዳር እፅዋት፣ ረግረጋማ ቦታዎች እና ዛፍ የበዛባቸው ሳቫናዎች ይገኙበታል። የባዮስፌሩ መመዝገብ የሀገሪቱን የጥብቅ ቦታ ሽፋን የሚያሳድግና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ሥራን ለዓለም ለማጋራት የሚያስችል መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት የደንና ግጦሽ መሬት ብዝሃ ሕይወት ምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበራ ስዩም ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባዮስፌር ለተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ለሰዎች የልማት ተጠቃሚነት ሚና አለው። ይህም ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ፣ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና ምርምርና ጥናት ለማካሄድ ሥራ ላይ ይውላል ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ሁለት ዓመታት የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭን ለማስመዝገብ ሲሠራ መቆየቱን አንስተው፤ ዘንድሮ በቻይና በተካሄደው ጉባዔ በዩኔስኮ ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል። የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭ ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር በላይ ስፋት ያለው፣ እምቅ የብዝሃ ሕይወት ሃብትና የማኅበረሰብ ተፈጥሮን የመጠበቅ ባህልን አጣምሮ የያዘ የጥበቃ ስፍራ ነው ብለዋል። የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭ መመዝገብ የሀገሪቷን ጥብቅ ቦታዎች አሁን ካለበት 12 በመቶ ወደ 30 በመቶ በማሳደግ ዓለም አቀፍ ግብ ለማሳካት እገዛ ያለው መሆኑን አቶ አበራ ተናግረዋል። የአኙዋ ባዮስፌር መመዝገብ ኢትዮጵያ ያላትን ፀጋ ለዓለም ይዛ የቀረበችበትና ለሀገር ገጽታ ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ምቹ ፖሊሲ፣ የብዝሃ ሕይወት ሃብትና የማኅበረሰብ ዕውቀት በማቀናጀት የተፈጥሮ ሃብት በመጠበቅ ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ያስቻላትን ልምድ ለዓለም የምታካፍልበት መሆኑንም አብራርተዋል። የአኙዋ ባዮስፌር መመዝገብ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም እና ኢትዮጵያ ለያዘችው የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ጠቀሜታ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል። በተያዘው የ2018 በጀት ዓመት ሁለት ተጨማሪ ባዮስፌር ሪዘርቮችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ በበኩላቸው፤ የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭ መመዝገብ የአገሪቱን የጥበቃ ቦታ ሽፋን የሚያሳድግ ነው ብለዋል። የአኙዋ ባዮስፌር፣ የካፋ፣ የሸካ፣ የያዩ፣ የጣና ሐይቅ እና የመጀንግ ደን ባዮስፌር ሪዘርቮችን በመቀላቀል በዩኔስኮ እውቅና ያገኘ የኢትዮጵያ ስድስተኛው ባዮስፌር ሪዘርቭ ነው።
ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው
Oct 29, 2025 243
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚችል ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደርና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ አኒል ኩማር ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በብዝሃ የአየር ንብረት የታደለች፤ ልዩ ልዩ የተፈጥሮ ሀብቶችን የያዘች፣ በርካታ እፅዋቶችና የዱር እንስሳት ዝርያዎች የሚገኙባት መሆኗን አምባሳደሩ ተናግረዋል፡፡ አምባሳደሩ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚችል ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ የአገሪቱን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ ለብዝሃ ህይወት መጎልበት ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ስራው አስደናቂ መሆኑን ተናግረዋል። በአፋር ክልል የሚገኘው ዝቅተኛው የደናክል በረሃ እና የተለየ የአየር ንብረት ያለው የስምጥ ሸለቆ መነሻ ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ አረንጓዴ የሆኑና ከፍተኛ የዝናብ መጠን የሚያገኙ ደጋማ አካባቢዎችን የያዘች መሆኗንም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያሉ ልዩ ልዩ የአየር ንብረት ጸባዮች፣ የዕጽዋትና የዱር እንስሳት ዝርያዎች ሀገሪቱን ብዝሃ ተፈጥሮ የተቸራት አድርጓታል ብለዋል፡፡ ይህም የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስፋት ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አመላክተዋል፡፡ አምባሳደሩ በኢትዮጵያ የተተገበሩ እንደ አረንጓዴ አሻራ ያሉ መርሃ-ግብሮችና ሰፋፊ የልማት ስራዎች ለሀገሪቱ የወደፊት ብልፅግና ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው ጠቅሰው ፤ የተተከሉት ዛፎች እንዲጸድቁ የሚደረገውን እንክብካቤ አድንቀዋል። በቀጣዩች አስር ዓመታት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደማሚ ለውጦችን ታስመዘግባለች ሲሉም ገልጸዋል። ህንድ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ለምታከናውነው ተግባር አድናቆት እንዳላት ጠቁመው፤ አገራቸው በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ አስፈላጊነት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ አቋም እንዳላት ተናግረዋል፡፡ ህንድ እና ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ የጋራ ስምምነት እንዳላቸው አስታውሰው፡ ትብብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ያከናወነቻቸው ተግባራት የአዕዋፋትንና የዱር እንስሳትን ስደት ትርጉም ባለው መልኩ መቀነሱ ይታወቃል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 207
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል። ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
Oct 31, 2025 194
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው
Oct 24, 2025 463
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡ ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡ በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀመረ
Oct 24, 2025 352
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦11ኛው የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተሞች በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው። በፎረሙ ላይ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች ምክክር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ሐተታዎች
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 23
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
የብዙዎች ቤት…
Oct 27, 2025 389
እስካሁን በተደረገ የጥናት ውጤት መሠረት ከ81 በላይ የአጥቢ እንስሣት፣ ከ450 በላይ የአዕዋፍ እና ከ400 በላይ የእፅዋት ዝርያዎች መኖሪያ ነው። ከእነዚህ መካከል አምስቱ የአዕዋፍ ዝርያዎች በዚህ ሥፍራ ብቻ ይገኛሉ፤ ከአምስቱ መካከል በተለይም የአንዷ ዝርያ ዓለም አቀፍ የዘርፉ ተመራማሪዎችንና ጎብኚዎች ቀልብ መሳቡ ይጠቀሳል። ከአካባቢው ተፈጥሯዊ አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ጋር መጣጣም የቻሉ የቆላ እፅዋት (ዛፎች) በምቾት በስፋት እንደሚገኙበትም ይገለጻል። የተመሠረተው በ1958 ዓ.ም ሲሆን፤ ስፉቱም 591 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ነው፤ በቁጥርም ሆነ በሥብጥር የብዙዎች መኖሪያ የሆነው ይህ ሥፍራ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ይሰኛል። መንግሥት በሰጠው ትኩረት ከነበረው በተሻለ ሁኔታ እንስሣቱም ሆኑ እፅዋቱ እየኖሩ ነው፤ ከሕገ ወጥ ድርጊትም እንዲጠበቁ ማድረግ መቻሉን የፓርኩ ኃላፊ አደም መሐመድ ለኢዜአ አረጋግጠዋል። በፓርኩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁንም ለ247 ወገኖች ቋሚ እና ለ2 ሺህ 535 ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ባሳለፍነው ዓመትም በ1 ሺህ 751 የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች እንደተጎበኘ ኃላፊው ገልጸዋል።
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 784
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል። ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው። የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው። ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል። ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 754
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም። በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል። የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል። በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል። በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል። በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1642
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2072
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2931
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3038
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 929
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 656
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6495
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4971
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የዳሰነቾች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ''
Oct 30, 2025 740
የዳሰነች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ'' (በጣፋጩ ሰለሞን ከጂንካ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ዳሰነቾች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በአብሮነት ተጎዳኝተው ይኖራሉ። የብሔረሰቡ አባላት ዋነኛ መተዳደሪያ ከብት እርባታ ሲሆን፤ ከከብት እርባታው ጐን ለጐን በዝቅተኛ ደረጃ በግብርናና በዓሳ ማስገር ስራ ይተዳደራሉ፡፡ ዳሰነቾች በሰሜን ከሐመር፣ በደቡብ ከኬኒያ፣ በምስራቅ ከቦረና በስተ ምዕራብ ደግሞ ከኛንጋቶም ማህበረሰብ ተጎራብተው ይኖራሉ። ዳሰነቾች ከኩሽቲክ የቋንቋ ነገድ የሚመዘዝ ''አፍ ዳሰነች'' የተሰኘ የመግባቢያ ቋንቋም አላቸው። ዳሰነቾች የተለየ የአለባበስ፣ የአጋጌጥ፣ የቤት አሰራር እና የባህላዊ የሙዚቃ ስልተ ምትን ጨምሮ አስደማሚ ባህሎች እና ማራኪ የመልክዓ ምድር አቀማመጥን የታደሉ ናቸው። ዳሰነቾች ከሚታወቁባቸው አስደማሚ ባህሎች ውስጥ አንዱ የሆነው አለመግባባቶችን በውይይት የሚፈቱበት የ''ጀለባ''ስርዓት ተጠቃሽ ነው። ይህ ስርዓት ግጭቱ ቂምና ቁርሾ በማይሻገርበት መልኩ በዘላቂነት የማስወገድ አቅም ያለው ሲሆን የማይናወጥ ሰላምና ወንድማዊ ትስስር እንዲጠናከርም ሚናው የጎላ ነው። ዕሴቱ የዳሰነቾች የአኗኗር ቁመና የሚለካበትና የሚመዘንበት መጻኢንም የሚተለምበትም ጭምር ነው። ስለሆነም በዳሰነቾች ዘንድ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል ነው የሚባለው። የባህሉ ተመራማሪ ሊዮን አርሎት 'ጀለባ'' የተሰኘው ባህላዊ ዳኝነት ከአካባቢው ሰላም አልፎ ለቀጠናው ወንድማማችነት መጠናከር ትልቅ ሚና ያለው የፍትህ ስርዓት መሆኑን ያነሳሉ። በ''በጀለባ'' ስርዓት ባህላዊ የዳኝነት አሰጣጥ እርከኖች እንዳሉ ጠቅሰው፥ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ ''ኖሞ'' የተሰኙ ሽማግሌዎች ወደ ስፍራው በማቅናት የግጭቱን መንስኤ በማጣራት ''ቶሎል'' ለተሰኙ ሌሎች ሽማግሌዎች የሚያሳውቁበት አሰራርም አላቸው። እንደ ግጭቱ ቅለትና ክብደት ''ቶሎል'' በተሰኙ ሽማግሌዎች ተለይቶ ቀለል ያለው ''ካባና'' በተሰኙ ዳኞች ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን፥ ጉዳዩ ከበድ ያለ ከሆነ ደግሞ የመጨረሻው ውሳኔ ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች ይሰጣል። ከነፍስ ማጥፋት በስተቀር ሁሉም ውሳኔዎች ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች እልባት ያገኛሉ። የነፍስ ማጥፋት ወንጀል ሲከሰት ግን ጉዳዩን ለመንግሥት አሳልፎ በመስጠት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያገኝ ይደረጋል ። ነፍስ ያጠፋው ሰው የእርምት ጊዜውን አጠናቆ ማህበረሰቡን ለመቀላቀል ሲወስን ባህላዊ የዕርቅ ስነ-ስርዓት ተዘጋጅቶ በዳይና ተበዳይ ይቅር የሚባባሉበትም ስርዓት እንዳለ የባህሉ ተመራማሪ ይናገራሉ። በዳሰነቾች ባህል ልዩነቶች ሰላማዊ በሆነ መንገድ በዘላቂነት መንገድ የመፍታት ዘመናትን የተሻገረ ድንቅ ዕሴት መኖሩን የሚያነሱት የብሔረሰቡ አባል አሸቴ ነካሲያ፤ “በዳሰነች ብሔረሰብ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል'' ይላሉ። በዳሰነቾች አለመግባባቶች በውይይት የሚፈቱበት ስርዓት እንዳለ ጠቅሰው፥ ''ናብ'' በተሰኘው የዳኝነት ስፍራ አለመግባባቶች ውለው ሳያድሩ እልባት ያገኛሉ ብለዋል። ሌላው የብሔረሰቡ አባል ሎቶያቡስ ሎኪሰሬሬ በበኩላቸው የባህል መሪዎች የተጣላን ማስታረቅ፣ ትውልዱን የመግራትና በስነ-ምግባር የማነፅ ኃላፊነት እንዳላቸው ጠቅሰዋል። ''ማንም ሰው ከባህል መሪዎች ትዕዛዝ አያፈነግጥም'' የሚሉት አቶ ሎቶያቡስ፥ ሁሉም እርስ በእርስ በመከባበር እና ችግሮች ሲኖሩ በውይይት በመፍታት አብሮነቱን ያጠናክራል ብለዋል። ወጣቱ ለባህል መሪዎች ታዛዥ ነው የሚሉት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ የብሔረሰቡ አባል ሎሲያ ሎብቻ ወጣቶች ለአካባቢው ሰላም ዘብ እንዲቆሙ፣ ከአጎራባች ህዝቦች ጋር በፍቅር እንዲኖሩ በማስተማር ወጣቱን በስነ-ምግባር የማነፅ ስራ እንደሚሰሩም ተናግረዋል። የዳሰነች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ በበኩላቸው የዳሰነች ህዝብ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ከወረዳው አልፎ ለቀጠናው ሰላም ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። የብሔረሰቡ ባህላዊ የሽምግልና ስርዓት ትውልዱን በመግራት በስነ- ምግባር የታነፀ ዜጋ እንዲፈጠር እንዳደረገም አስረድተዋል። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የሶሻል አንትሮፖሎጂ መምህርና ተመራማሪ አጎናፍር ሰለሞን፤ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓቶች ለዘመናዊው የፍትህ ስርዓት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል ብለዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች ቅጣት በመጣል ጥፋተኝነት እንዲሰማ የሚያደርጉ ሳይሆኑ፤ እውነተኛ ይቅርታን የሚያሰፍኑና ለአብሮነት የሚበጁ ዕንቁ ባህሎች እንደሆኑም አብራርተዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹ በግለሰብ ተጠቃሚነት ላይ ሳይሆን በማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት የሚያደርጉ በመሆናቸው ከዘመናዊው የፍትህ ስርዓት በይበልጥ ለአብሮነት መጠናከር አስተዋጽኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹም ለሀገራዊ መግባባት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ፥ እሴቶቹ ተጠብቀው፣ ለምተውና ጎልብተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት እንደሚገባም መክረዋል። ሀገራችን ቂምና ቁርሾን የወለዱ ያለመግባባቶች በዘላቂነት በሰለጠነና ሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ሁሉንም ያሳተፈ ስራ እየሰራች እንደሆነ ያነሱት መምህርና ተመራማሪው አጎናፍር ሰለሞን ዕሴቶቹ በማህበረሰቡ ዘንድ ካላቸው ተቀባይነት እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ሂደቱን ከማገዝ አንጻር ጉልህ ሚና ስለሚኖራቸው መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
''ቦር ተራራ'' የየሞች የፈውስ ምድር
Oct 27, 2025 414
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) የም ዞን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ይገኛል። በዞኑ የቦር ተራራ ዋነኛው የመድኃኒት እጽዋት መገኛ እና ምንጭ በመሆኑ የሞች በየዓመቱ ጥቅምት ወርን ጠብቀው በ17ኛው ቀን ከዚህ ተራራ በህብር ሆነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስነ-ስርዓት ያካሂዳሉ፤ ይሰባስባሉም ። የቀደምት የየም አባቶችና እናቶችን በማሳተፍ የሚከወነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ከባህር ጠለል በላይ 2 ሺህ 939 ሜትር ከፍታ ላይ በሚገኘው ቦር ተራራ ላይ ነው። በዚህ ተራራ ላይ በየዓመቱ ጥቅምት 17 ቀን የሞች ለዓመት የሚያገለግላቸውን የመድኃኒት እጽዋት ይለቅማሉ። ተግባሩንም አዋቂዎች በጋራ ሰብሰብ ብለው ለመድኃኒት የሚውለውን ቅጠል በጥሰው፣ ስር ምሰው፣ አስሰውና መርጠው ይሰበስባሉ። ይህም የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስርዓት "ሳሞ ኤታ" ተብሎ ይጠራል ። አያምጣውና ህመም ሲከሰት ታማሚውን ሰው ወይም እንስሳን ከበሽታው ለመፈወስ የተዘጋጀው ባህላዊ መድሃኒት በባህላዊ ሃኪም ትዕዛዝ መሰረት በህመሙ ልክ ይታዘዝለታል። መድሃኒቱን ለመጠቀምም የጠቢባን አባቶችን ፈለግ ተከትሎ መፈፀም የግድ ይላል። የሞች አጅግ አስገራሚ እና አስደናቂ የሆኑ የበርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤት ናቸው ካስባሏቸው እሴቶች መካከል ይህ ለየት ያለው ክዋኔያቸው አንዱ ነው፡፡ አባቶች ታዳጊና ወጣቶችን አስከትለው ወደ ቦር ተራራ በመውጣት የሚፈፅሙት ባህላዊ ክዋኔ በመሆኑም ከትውልድ ወደ ትውልድ ቅብብሎሹን ጠብቆ እስከ አሁን እንዲዘልቅ እድርገውታል። በየሞች ዘንድ የባህላዊ መድኃኒት አዋቂዎች ከሚባሉት መካከል አንዱ አቶ ጌታቸው ሃይለማርያም፤ የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ልምድን የቀሰሙት ከአባታቸው መሆኑን በመግለፅ አያታቸው ከቅድመ አያቶቻቸው በመውረስ እዚህ እንዳደረሱት ይናገራሉ። የቦር ተራራ ለመድሃኒት ዕፅዋት ለቀማው የተመረጠበትን ምክንያት ሲያስረዱም ቦታው ተራራ በመሆኑ ማንም ያልደረሰባቸው የተለያዩ እፅዋትን ለማግኘት አመቺ ከመሆኑ ጋር ያያይዙታል። በሌላም በኩል ጠዋት ፀሐይ ስትወጣ መጀመሪያ የምታገኘው ተራራውን በመሆኑና ክረምቱ አልፎ ጥቅምት ሲገባ የተለያዩ ቅጠላ ቅጠሎችን በብዛት እና በዓይነት ለማግኘት ተመራጭ ወቅት መሆኑም ቦታው የተመረጠበት ሌላኛው ምክንያት ነው ብለዋል። በጥቅምት 17 ለመድኃኒትነት የሚያገለግለው ዕፅዋት ቅጠልም በየፈርጁ ተለቅሞ እና ተቀምሞ ይቀመጣል ሲሉም አስረድተዋል። የተዘጋጀው ባህላዊ መድኃኒትም ለሰው ልጆችና ለቤት እንስሳት ያገለግላል ሲሉም አስረድተዋል፡፡ ይኸው በዚህ ቀን የተለቀመው የመድኃኒት ዕፅዋት ከዚህኛው ጥቅምት 17 እስከሚቀጥለው ዓመት ጥቅምት 17 ድረስ እንደሚያገለግልም አቶ ጌታቸው አስረድተዋል፡፡ የባህል መድኃኒት ሰብሳቢዎች እና ተጠቃሚዎች ጊዜውን ጠብቀው ከተለያዩ ቦታዎች ወደ ቦር ተራራ እንደሚመጡ የሚገልጹት የባህል መድኃኒት አዋቂው ዛሬ ዛሬ እሳቸውን ጨምሮ መድኃኒት ቤቶችን በመክፈት ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ የባህል መድኃኒቶችን በመሸጥ ኑሯቸውን እየመሩ የሚገኙ አያሌ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉም ይናገራሉ። ሌላኛው የባህል መድኃኒት አዋቂው አቶ ወልደመስቀል ጆርጋ በበኩላቸው በየሞች ዘንድ የተዘጋጀው የመድኃኒት ዕፅዋት ጥቅም ላይ የሚውለው ህመም ሲያጋጥም ብቻ ሳይሆን በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል መሆኑን ጠቁመው መድኃኒቶቹም ብቻቸውን እንዲሁም ከምግብ ጋር በመመገብ ለጥቅም እንደሚውሉም አንስተዋል። የየም ምድር የበርካታ የመድኃኒት ዕፅዋቶች መገኛ አካባቢ " የፈውስ ምድር " ነው የሚሉት ደግሞ በየም ባህላዊ መድኃኒት ዙሪያ ጥናት ያደረጉት በጅማ ዩኒቨርሲቲ የፎክሎር መምህር እና ተመራማሪ ለማ ንጋቱ (ዶ/ር) ናቸው። ከየሞች አያሌ የባህል ዕሴቶች መካከል የባህል መድኃኒት ለቀማና ቅመማ አንዱና ዋነኛው የሀገር በቀል እውቀት ማሳያ መሆኑን ገልፀው የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ስነ-ስርዓቱ ከጥንት ጀምሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ዛሬ ላይ የደረሰ እንደሆነም ያስረዳሉ፡፡ ማህበረሰቡ የራሱንም ሆነ የእንስሳትን ጤና የመጠበቅ የቆየ ባህል ያለው መሆኑን በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው የባህላዊ መድኃኒት ለቀማው ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚሳተፉበት ዓመታዊ ክዋኔ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ሌላው ገራሚው ነገር ይላሉ አጥኚው ታላላቆች ታናናሾቻቸውን አስከትለው የለቀማ ሂደቱን የሚያስረዱበት መንገድ ደግሞ ስርዓቱ ለመጪው ትውልድ እንዲተላለፍ የሚያስችል ትውልድ ተሻጋሪ የሀገር በቀል እውቀት ሽግግር ስርዓት ማሳያ እንደሆነም ነው የገለጹት። በዚህም ሂደት የሚነገሩ ስነ-ቃሎች መሞጋገስ፣ ጭፈራና ደስታ ይስተናገድባቸዋል። ይህም ማህበራዊ ትስስርን ይበልጥ የሚጠናክሩበትን ሁነት የሚፈጥር ስርዓት ነው። የየም ዞን ባህል እና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ሞጋ በበኩላቸው የቦር ተራራ የመጀመሪያውን የማለዳ የፀሐይ ጎህ የሚፈነጥቅበት የንጋት ብርሃን ቀድሞ የሚያገኝ በመሆኑ፥ በዚህ አካባቢ የሚገኙ እጽዋት በሽታን የመከላከልና ፈዋሽነታቸው ከፍተኛ ነው ተብሎ ስለሚታመን ለዚህ ክዋኔ ቦታው መመረጡን ነው የሚገልፁት። ለዚህም ነው የሞች ይህንን ስፍራ ከሌሎች ቦታዎች አስበልጠው የሚወዱት፤ በየዓመቱም ጥቅምት 17 ቀን ወደ እዚህ ስፍራ በማቅናት ለዓመት ፍጆታ የሚያገለግላቸውን መድኃኒትም ይሰበስቡበታል ብለዋል። ጥቅምት 17 በየም ዘንድ ለየት የሚያደርገው ሌላው የመድሃኒት ዕፅዋት ለመልቀም እና ለመጠቀም ብቻ ሳይሆን የለቀማውን ትዕይንት ለመመልከት የሚመጡ ቱሪስቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸው ሌላው ትልቁ ትሩፋት ነው ይላሉ። የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማው ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት በመሆኑ፥ ለአብሮነት እና ሃገር በቀል እውቀት ለመቅሰም ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ነው አቶ መስፍን የገለፁት።