ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በጠቅላላ ምርጫው የወጣቶችን ተሳትፎ ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጓል
May 14, 2026 2
ጭሮ /ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በጠቅላላ ምርጫው የወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ወጣቶች ማህበር አስታወቀ። የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እና ለሀገር መፃኢ ዕድል ቁልፍ መሣሪያ ነው። በዞኑ ወጣቶች በምርጫው ሂደት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የምርጫ ካርድ እንዲወስዱ ሰፊ ቅስቀሳ ተደርጓል። የወጣቶችን የምርጫ ተሳትፎ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ወጣቶች በታዛቢነት እና በምርጫ አስፈጻሚነት እንዲሳተፉ በማድረግ የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እየተሰራም ይገኛል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ወጣቶች ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ሙርቴሳ መሐመድ እንደገለፁት፤ በጠቅላላ ምርጫው እውን በሚሆነው የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የወጣቶችን ተሳትፎ ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጓል። ወጣቱ በዕውቀት ላይ ተመስርቶ እንዲመርጥ እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እየተሰጠ ነው ብለዋል። ምርጫ ለሰላምና ለዴሞክራሲ ግንባታ መሰረታዊ ጉዳይ በመሆኑ ወጣቱ በንቃት በመሳተፍ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ለዚህም ማህበሩ ግንዛቤ ከመስጠት ባለፈ፣ በዞኑ በሚገኙ 15 ወረዳዎችና 5 ከተሞች ውስጥ ሂደቱን የሚከታተሉ 2 ሺህ 756 የምርጫ ታዛቢዎችን መድቧል ነው ያሉት። ወጣቱ የአንድ ሰው ድምጽ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለውን ወሳኝነት በመረዳት በካርዱ የሚበጀውን የፖለቲካ ፓርቲ በዕውቀት እንዲመርጥም ጥሪ አቅርበዋል። ከጭሮ ከተማ ወጣቶች መካከል ወጣት አብደላ መሐመድ እና ወጣት መሐመድ ሐሰን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በከተማው ወጣቶች ማህበር በኩል በተፈጠረው ግንዛቤ የምርጫ ካርድ በመውሰድ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል። በምርጫ ካርዳቸው ለሀገር ግንባታ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥም በመገናኛ ብዙሃን እና በተለያዩ አማራጮች የሚደረጉ የምርጫ ቅስቀሳዎችን እየተከታተሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በኦሮሚያ ክልል በመኽር እርሻ እስካሁን 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት ታርሷል
May 14, 2026 22
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለ2018/19 የምርት ዘመን በመኽር እርሻ ከታቀደው ውስጥ እስካሁን 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት ታርሶ ለዘር መዘጋጀቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ መንግስት በየዓመቱ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለአፈር ዝግጅት፣ ለግብዓት አቅርቦትና ለቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሀላፊ በሪሶ ፈይሳ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ በክልሉ በዘንድሮ የመኽር እርሻ 11 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች በማልማት 367 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል። ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለግብርና ዘርፉ በተሰጠው ትኩረት ከአርሶ አደሮች ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የዘርፉ አመራርና ባለሙያ እቅድ በማውጣት በውይይት ተጠናክሮ የማሳ ዝግጅት በከፍተኛ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በዘር ለመሸፈን ከታቀደው 11 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታሩ ታርሶ ለዘር መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እስካሁን ከታረሰው መሬት ውስጥም አንድ ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑንም አክለዋል። በክልሉ በአሁኑ ጊዜ የዝናብ ሁኔታው ጥሩ ደረጃ ላይ በመሆኑ በተለይም በምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢዎች በአራቱ የወለጋ ዞኖችና ጅማና ኢሉባቦር ዞኖች ቀድመው የሚደርሱ እንደ በቆሎ፣ በሀረርጌ አካባቢዎች ደግሞ የማሽላ ሰብሎች ዘር መዝራት ተጀምሯል ብለዋል። ከታቀደው ማሳ ከስድስት ሚሊየን ሄክታር መሬት በላይ በትራክተር የሚታረስ መሆኑን አንስተው፣ ልማቱ በኩታ ገጠም እንደሚከናወንም ገልጸዋል። በክልሉ በቂ የግብዓት አቅርቦት መኖሩን ጠቅሰው፣ በአሁኑ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ እና 300 ሺህ ኩንታል የሚሆኑ የተለያዩ አይነት ምርጥ ዘሮች በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች መድረሱን አንስተዋል። በኦሮሚያ ክልል ዘንድሮ ለአጠቃላይ የግብርና ልማቱ 10 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያና ከሁለት ሚሊየን ኩንታል በላይ የተለያዩ ምርጥ ዘሮች ጥቅም ላይ እንደሚውሉም ተናግረዋል።
ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድን ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከመቀሌ 70 እንደርታ በኢትዮጵያ ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ ይገናኛሉ
May 14, 2026 41
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ድልድል ዛሬ የክለብ ተወካዮች እና የውድድር አመራሮች በተገኙበት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽሕፈት ቤት ወጥቷል። በእጣው መሰረት ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድን ፣ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ መቀሌ 70 እንደርታ የሚጫወቱ ይሆናል። የጨዋታ ቀናት ወደፊት እንደሚገለጽ ፌዴሬሽኑ አስታውቋል።
አዲስ አበባ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን ከከተማ ፕላንና ልማት ጋር በማቀናጀት መተግበሯ በአርዓያነት የሚጠቀስ ነው
May 14, 2026 90
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን ከከተማ ፕላንና ልማት ጋር በማቀናጀት መተግበሯ በአርዓያነት የሚጠቀስ አስደናቂ ተግባር ነው ሲሉ ዓለም አቀፍ ተመራማሪዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎች ግንባታ ለሌሎች የዓለም ከተሞች አርዓያ የሚሆኑ መሆናቸውንም ተናግረዋል። አዲስ ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ “አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ሥርዓት ለውጥ የግንባር ቀደምትነት ሚና፤ ከአካባቢያዊ ሞዴሎች ወደ ዓለምአቀፍ እንቅስቃሴ” በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡ በዚህም ከፅንስ እስከ ስድስት ዓመት የዕድሜ ክልል የሚደረግ ስኬታማ ኢንቨስትመንት አዲስ አበባን የአፍሪካ ተመራጭ የህፃናት ማሳደጊያ ከተማ እያደረጋት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ በአዲስ አባባ እየተከናወነ ያለውን የቀዳማይ ልጅነት ልማት በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት ተመራማሪዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች፤ ከተማዋ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ከከተማ ፕላንና ልማት ጋር አስተሳስራ እየሰራች ያለችበት መንገድ አስደናቂ ነው፡፡ በፈረንሣይ ሬንስ ዩኒቨርሲቲ የወላጆች አዕምሮ ተመራማሪ ጆዲ ፓውሉስኪ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በአዲስ አበባ እየተተገበሩ ያሉ ፈጣን የልማት ስራዎች የከተማ እድገት ለህፃናት ደህንነትና ለጤና አስፈላጊ የሆኑ መሠረታዊ ጉዳዮችን እንዴት ማካተት እንዳለበት የሚያሳይ ትልቅ ምሳሌ ናቸው፡፡ ከተማዋ ደህንነቱ የተጠበቀ አካባቢን፣ አረንጓዴ ቦታዎችንና የመጫወቻ ስፍራዎችን በማስፋፋት በኩል ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለችም ብለዋል። ይህም ለቤተሰቦች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ፣ ሌሎች የዓለም ከተሞችም የአዲስ አበባን ተሞክሮ በመቀመር በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ እነዚህ የልማት ስራዎች ለህፃናት እድገትና ለአጠቃላይ ማህበረሰቡ ጤና የሚኖራቸው ሚና እጅግ አስፈላጊ እንደሆነም ነው የጠቆሙት፡፡ የከተማ ፕላኒንግ እና አርክቴክቸር ፕሮፌሰር የሆኑት አሩናቫ ዳስጉፕታ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አዲስ አበባ ለህፃናት ምቹ የሆኑ ስፍራዎችን ለመፍጠር የሚታዩና ተግባራዊ የሆኑ በርካታ አበረታች እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች ብለዋል፡፡ ከተማዋ እያሳየችው ያለው ጠንካራ ቁርጠኝነት እና የተጀመሩ ተነሳሽነቶች አሁኑኑ በግልጽ በስራ እየታዩ መሆናቸው ለሌሎች የአፍሪካ ከተሞች ትልቅ ተሞክሮ እንደሚሆኑ ገልጸዋል፡፡ የአዲስ አበባ ተሞክሮ ሌሎች የዓለም ከተሞች በፍጥነት ሊቀስሙት የሚገባ ጠንካራ ምሳሌ መሆኑም ጠቅሰዋል፡፡ በሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የህፃናት እድገት ማዕከል ከፍተኛ ባልደረባ የሆኑት ጄምስ ኬርንስ እንዳሉት፤ በአዲስ አበባ የቅድመ ሕፃናት እንክብካቤ ተነሳሽነት ከኮሪደር እና ከአረንጓዴ ልማት ጋር መቀናጀቱ ከተማዋን ለቤተሰብ ምቹ የማድረግ ስትራቴጂ አካል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በከተማው ለሕፃናትና ለቤተሰቦች ደጋፊ የሆነች ከተማን ለመፍጠር በወላጆች አማካሪዎች፣ በሕፃናት ማቆያ ማዕከላትና በመጫወቻ ስፍራዎች ግንባታ ላይ የተመዘገበው እድገት እጅግ አስደናቂ መሆኑ ተናግረዋል፡፡ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ለልጆች እድገት አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶች በጥሩ ሁኔታ እንዲገነቡ መደረጉ ለከተማዋ የልማት ዕቅድ መጠናከር እንደ ጠንካራ ምሰሶ ተጠቃሽ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትን በማጎናጸፍ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ የሚገኘው አራዳ ፓርክ
May 14, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ የተገነባው አራዳ ፓርክ የቀድሞ ፒያሳ ገጽታን በመቀየር ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትን በማጎናጸፍ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ የሚገኝ ምቹ የመዝናኛ ስፍራ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ጉብኚዎችና ወጣቶች ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ በጥራትና በፍጥነት የተገነቡ ፓርኮች፣ የኮሪደርና የወንዝ ዳር ልማቶች መዲናዋን ዘመናዊና ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛሉ። አዲሱ አራዳ ፓርክ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ከተደረገ ወዲህ በርካታ ጎብኚዎች ስፍራውን እየጎበኙ ይገኛሉ። ኢዜአ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት በመዲናዋ የተሠሩት የልማት ስራዎች የከተማዋን እድገትና ለውጥ ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። በአራዳ ፓርክ ጉብኝት ሲያደርጉ ያገኘናቸው አቶ ካሳሁን ሙላት፤ በአዲስ አበባ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ሕፃናትን፣ አዋቂዎችንና ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች ያማከሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህ አስደናቂ ልማት ለአሁኑ ትውልድ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱም ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመው ስኬቶቹ የኅብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። ሌላኛዋ የፓርኩ ጎብኚ ተማሪ ማያ ጆን በበኩሏ፤ በመዲናዋ በመንግሥት የተገነቡ ልዩ ልዩ ፓርኮችን መጎብኘቷን አስታውሳ የአራዳ ፓርክ በዓይነቱ ለየት ያለና ማራኪ ገጽታ የተላበሰ ስፍራ ሆኖ እንዳገኘችው ተናግራለች። እነዚህ የልማት ሥራዎች የመዲናዋን ገጽታ ከመለወጥ ባለፈ ለወጣቱ ትውልድ ምቹና ብሩህ ተስፋ የምታሰንቅ ከተማ ለመፍጠር ያስችላሉ ስትል ገልጻለች። ከሐረር ከተማ የመጡትና ፓርኩን ሲጉበኙ ያገኘናቸው አቶ ማሂር ከማል፤ ስፍራው ከጠበቁት በላይ እጅግ አስደናቂ ገጽታ ተላብሶ እንዳገኙት ተናግረዋል። በተለይም በፓርኩ ውስጥ የተገነቡት ዘመናዊ የእግረኛና የሳይክል መንገዶች፣ ማራኪ መናፈሻዎችና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ለጎብኚዎች ልዩ እርካታ እንደሚሰጡ አብራርተዋል። ከልጆቻቸው ጋር በአራዳ ፓርክ ሲዝናኑ ያገኘናቸው አቶ ከማል ሸሞሎ በበኩላቸው፤ መዲናዋ ቀደም ሲል የነበረባትን የመጫወቻ ስፍራ እጥረት በመቅረፍ ለሕፃናት ምቹ አማራጮችን መፍጠር መቻሏን ገልጸዋል። ይህም ሕፃናት በቂ እና ምቹ የመዝናኛ ስፍራ እንዲያገኙ እና አካላዊና ሥነ-ልቦናዊ እድገታቸው ተስተካክሎ እንዲያድጉ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።
ፖለቲካ
በጠቅላላ ምርጫው የወጣቶችን ተሳትፎ ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጓል
May 14, 2026 2
ጭሮ /ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በጠቅላላ ምርጫው የወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ወጣቶች ማህበር አስታወቀ። የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እና ለሀገር መፃኢ ዕድል ቁልፍ መሣሪያ ነው። በዞኑ ወጣቶች በምርጫው ሂደት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የምርጫ ካርድ እንዲወስዱ ሰፊ ቅስቀሳ ተደርጓል። የወጣቶችን የምርጫ ተሳትፎ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ወጣቶች በታዛቢነት እና በምርጫ አስፈጻሚነት እንዲሳተፉ በማድረግ የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እየተሰራም ይገኛል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ወጣቶች ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ሙርቴሳ መሐመድ እንደገለፁት፤ በጠቅላላ ምርጫው እውን በሚሆነው የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የወጣቶችን ተሳትፎ ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጓል። ወጣቱ በዕውቀት ላይ ተመስርቶ እንዲመርጥ እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እየተሰጠ ነው ብለዋል። ምርጫ ለሰላምና ለዴሞክራሲ ግንባታ መሰረታዊ ጉዳይ በመሆኑ ወጣቱ በንቃት በመሳተፍ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ለዚህም ማህበሩ ግንዛቤ ከመስጠት ባለፈ፣ በዞኑ በሚገኙ 15 ወረዳዎችና 5 ከተሞች ውስጥ ሂደቱን የሚከታተሉ 2 ሺህ 756 የምርጫ ታዛቢዎችን መድቧል ነው ያሉት። ወጣቱ የአንድ ሰው ድምጽ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለውን ወሳኝነት በመረዳት በካርዱ የሚበጀውን የፖለቲካ ፓርቲ በዕውቀት እንዲመርጥም ጥሪ አቅርበዋል። ከጭሮ ከተማ ወጣቶች መካከል ወጣት አብደላ መሐመድ እና ወጣት መሐመድ ሐሰን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በከተማው ወጣቶች ማህበር በኩል በተፈጠረው ግንዛቤ የምርጫ ካርድ በመውሰድ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል። በምርጫ ካርዳቸው ለሀገር ግንባታ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥም በመገናኛ ብዙሃን እና በተለያዩ አማራጮች የሚደረጉ የምርጫ ቅስቀሳዎችን እየተከታተሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ምርጫው ስኬታማ እንዲሆን የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
May 14, 2026 74
ደደር፤ ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፡- 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ስኬታማ እንዲሆን የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የደደር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የደደር ከተማ ነዋሪዎች፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልጸዋል። ነዋሪዎቹ ምርጫው ስኬታማ እንዲሆንና ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲከናወን ከሚመለከታቸው የሰላም፣ የቁጥጥርና ሌሎች አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ላይ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አባገዳ አብዱማሊክ ጁንዲ፤ ምርጫው ነፃና ሰላማዊ ሆኖ እንዲካሄድ የላቀ ድርሻና ኃላፊነት እንዳለባቸው በመገንዘብ እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው። ህዝቡ በምርጫው እንዲሳተፍ ለማድረግ ከሁሉም አካላት ጋር በመቀናጀት መስራታቸውን ጠቁመው፤ መራጩ ህዝብም በድምጽ መስጫ ወቅት ይበጀኛል ለሚለው ፓርቲ ድምጹን እንዲሰጥና ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። ምርጫው የዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብት ማረጋገጫ ነው ያሉት ደግሞ በደደር ከተማ በንግድ ስራ የሚተዳደሩት አቶ አብዱሹ አህመድ ናቸው። የመራጮች ምዝገባ መካሄድ ከጀመረበት እለት አንስቶ ህዝቡን የማንቃት ሥራ እየሰሩ መሆኑን አንስተው ምርጫው ያለምንም ችግር ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የበኩሌን እወጣለው ሲሉም አክለዋል። ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ አድናን ሻፊ በበኩላቸው፤ የምርጫውን እለት በጉጉት እየጠበቁና በተለይም ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ምርጫው ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲካሄድ እንዲሁም ወጣቶች በንቃት እንዲሳተፉ የበኩላቸውን ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን የጠቆሙት ደግሞ አቶ አብደላ አህመድ ነው። ለምርጫው ሰላማዊነትና ስኬት በተለይም ወጣቶችን በማስተባበር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
በወሰድነው የመራጭነት ካርድ ለሀገር ልማትና ዕድገት ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
May 14, 2026 72
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የወሰዱትን የመራጭነት ካርድ ለሀገር ልማትና ዕድገት ይበጃል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አስተያየት የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24/2018ዓ.ም መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ። የዘንድሮው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባም ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም የተከናወነ ሲሆን ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14/2018 ዓ.ም በማራዘም ተካሂዶ ተጠናቋል። በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ድምፅ መስጫ ካርድ ላልወሰዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች፣ በዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ ተማሪዎችና በካምፕ ለሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በልዩ ሁኔታ እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018ዓ.ም በማራዘም አጠናቋል። መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ከ50 ሚሊየን 514 በላይ መራጮች ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ መውሰድ ችለዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለምርጫ ታዛቢነት ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር ውስጥ ድርጅቶችም በተለያዩ አካባቢዎች ከ60ሺህ 277 በላይ ወኪሎችን አሰማርተዋል። በመራጮች ትምህርት ላይ ዕውቅና የተሰጣቸው 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ለመራጩ ህዝብ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርትና ስልጠና እየሰጡ ይገኛሉ። በአዲስ አበባ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመመዝገብ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ለሀገርና ለሕዝብ ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል። ከመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ወርቁ ፍቃዱ እንደገለጹት፤ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ካርድ ከማውጣት ጀምሮ የምርጫውን ቀን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ እየሩሳሌም ሀረገወይን በበኩላቸው፤ በምርጫ ካርዳቸው ለሀገር ልማትና ዕድገት ዕውን መሆን ለሚሰራ ፓርቲ ይሁንታ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ሌሊሳ ጋዲሳም እንዲሁ፤ የምርጫ ካርድ በማውጣት ለሀገር ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የድምፅ መስጫ ቀኑን እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል። የምርጫ ሂደትም ፍትሀዊ፣ ነጻ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። የመዲናዋ ነዋሪ ወደሬ ገብረጻዲቅ እንደተናገሩት፤ ምርጫ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን በመጠቆም፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅት አድርገዋል። አቶ ድሪቢሳ ጥሩነህ በበኩላቸው፤ ምርጫው ሕገ-መንግሥታዊ የመምረጥና መመረጥ ዴሞክራሲያዊ ማረጋገጫ ወሳኝ መድረክ በመሆኑ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገር ሰላም፣ ልማትና ዕድገት መረጋገጥ ለሚሰራ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት ከወዲሁ ተዘጋጅቻለሁ ያሉት ደግሞ አቶ ተሾመ አስፋው ናቸው።
ኢትዮጵያ የባለብዙ ወገን ግንኙነት እና ዓለም አቀፍ ትብብር ተምሳሌት ናት - የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ
May 13, 2026 474
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ትብብርና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ያላትን ቁርጠኝነትና ተምሳሌትነት አደነቁ። ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ አውጥታለች። የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሁነቱን በማዘጋጀታቸውና የኢትዮጵያ ህዝብ ላደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋና አቅርበዋል። ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሩ ለተመድ 80ኛ ዓመት ምስረታ ከመዘከር ባለፈ ተመድ እና ኢትዮጵያ ያላቸውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት የሚያሳይ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1945 ተመድ በሳን ፍራንሲስኮ ሲመሰረት ቻርተሩን ከፈረሙ 51 ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነች አውስተዋል። ኢትዮጵያ አሁን የባለብዙ ወገን እና ዓለም አቀፍ ትብብር ተምሳሌት ሆና መቀጠሏን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔን የምትወክል ሀገር ናት ያሉት ዋና ፀሐፊው በዓለም ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗንም አንስተዋል። እንደ ኢትዮጵያ ጠንካራ የታሪክ መሰረት ያላቸው ሀገራት መጻኢ ጊዜያቸው ጠንካራ እና ብሩህ እንደሆነ ገልጸዋል። አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ ገዢዎች ስር በነበሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ነጻነቷን አስጠብቃ የቆየች ሀገር መሆኗን ገልጸው ይህም የጥንታዊ ስልጣኔዋ ውጤት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነጻ ከወጡ በኋላ የተመድ አባል ሀገራት እንዲሆኑ ድጋፍ ማድረጓንም አስታውሰዋል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀማጫ በአፍሪካ የተመድ ከፍተኛ የተቋማት እና የሰራተኞች ብዛት ከያዙ ከተሞች መካከል እንደምትጠቀስም አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች በተመድ ጥላ ስር በሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ወሳኝ ሚና መጫወታቸውን አንስተውም በዓለም ላይ አደገኛና አስጊ የሚባሉ ቦታዎች በመሄድ መስዋዕትነት በመክፈል ሰላም እና መረጋጋት ለተወጡት ሚና ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ተመድ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ መከባበር መርህ ትብበሩን ማጠናከር እንደሚሻና አጋርነቱን ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆኑን አመልክተዋል። የተመድ ግብ የኢትዮጵያ ህዝብ ማገልገል እና የኢትዮጵያ መንግስት ስትራቴጂዎች እንዲሳኩ መደገፍ ነው ብለዋል። ተመድ ለኢትዮጵያ በሰላምና ደህንነት፣ በልማት፣ በሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት እና የተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ተመድ የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፍትሐዊ የዓለም አስተዳር ስርዓት እንዲሰፍን ያላቸውን ጥሪ እንደሚደግፍና ለስኬታማነቱም እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ማሻሻያ በማድረግ አሁናዊ የዓለም ሁኔታ እንዲያንጸባርቅ እና በአፍሪካ ላይ የደረሱ ታሪካዊ ኢፍትሃዊነቶች መካስ አለባቸው ብለዋል። አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና እንታገኝ በማድረግ የምክር ቤት ቅቡልነት እና ውጤታማነት ማሳደግ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጡም አንስተዋል። አፍሪካ የቅኝ ግዛት እና በዓለም ተቋማት ፍትሃዊ በሆነ ሁኔታ ያለመወከሏ ሁለት ጉዳት መሆኑን ያነሱት ዋና ፀሐፊው ኢትዮጵያ ከተመድ መነሻው የአፍሪካ ተወካይ መሆኗን አድንቀዋል። ተመድ ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሬፎርም እና የአፍሪካ የጸጥታው ምክር ቤት ውክልና እንድታገኝ ያቀረበችው ጥሪ ተገቢና ድርጅቱ ፍላጎቱ እውን እንዲሆን ይሰራል ብለዋል። አፍሪካ በዓለም የፋይናንስ ስርዓት ውስጥ ፍትሐዊ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባትና ውሳኔ ሰጪነቷ ሊያድግ እንደሚገባ አንስተዋል። ኢትዮጵያ ያሳተመችው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ተመድ እስከ አሁን የመጣበትን የሚያወሳ ከመሆን ባለፈ አሁን ዓለም ላይ የታጋረጡ ፈተናዎችን በጋራ መፍታት እንዳለብን የሚያሳስብ ነው ብለዋል። ሰላም፣ ፍትህ እና ብልጽግና ለሁሉም የሚለው የተመድ የጸና እሳቤ ትርጉም ያለው እና የማይተካ መሆኑን አንስተዋል። ለተሻለች አፍሪካ እና ዓለም መፈጠር በጋራ እንስራ ሲሉ ጥሪ ያቀረቡት አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፍትሐዊነት እና የዓለምን አሁናዊ ሁኔታ ያማከለ ለውጥ ያስፈልገዋል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
May 13, 2026 302
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፍትሐዊ፣ አካታች እና የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ያማከለ ለውጥ እንደሚያስፈልገው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ አውጥታለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመርሐ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 80ኛ ዓመት በሚከበርበት ወቅት የባለብዙ ወገን ተቋማት እየተለወጠች ካለው ዓለም ጋር አብረው መጓዝ እንዳለባቸው አጽንኦት መስጠት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል። ከ80 ዓመታት በፊት ከአስከፊው ጦርነት በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መቋቋሙን አውስተዋል። የተመድ መቋቋም ሀገራት በጋራ መርህ ለሰላም፣ ክብር እና መረጋጋት በትብብር መስራት አለባቸው ከሚለው እሳቤ የመነጨ መሆኑን አመልክተዋል። ይህ እሳቤ በተመድ ቻርተር ውስጥ መካተቱን ጠቅሰው ለሰብዓዊ ክብር፣ ፍትህ፣ እኩልነት እና ማህበራዊ ለውጥ የቻርተሩ ምሰሶዎች እንደሆኑ ነው ያነሱት። ኢትዮጵያ ከተመድ መስራች ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዓለም አቀፍ ስርዓት ውስጥ ያላት ታሪክ በመርሕ የተመሰረተ እና ከፍተኛ ፈተናን ያለፈ መሆኑን አመልክተዋል። የጋራ ደህንነት እሳቤ ውጤታማ ባልሆነበት የሊግ ኦፍ ኔሽን ውድቀት ኢትዮጵያ በወቅቱ መመልከቷን ጠቅሰው፤ ያ ታሪክ ኢትዮጵያ ለትብብር ጀርባውን እንዳትሰጥ ማድረጉን ነው ያነሱት። ኢትዮጵያ በወቅቱ ከነበረው ሁነት ትምህርት መውሰዷንና የተቋማት ተአማኒነት የሚለካው በፈተና ወቅት በሚሰጠው ምላሽ መሆኑን የጸና አቋም መያዟን ተናግረዋል። በሀገራት መካከል ያለ መተማመን ጫና ውስጥ ገብቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግጭቶች ይበልጥ እየተወሳሰቡ መምጣታቸውን አንስተዋል። በቃል ኪዳኖች እና በትበራዎች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ መምጣቱንም አስረድተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አሁናዊ የዓለም ሁኔታን ያማከለ፣ ፍትሃዊ እና አካታች በሆነ መልኩ ራሱን እየለወጠ መሄድ እንዳለበትም አስገንዝበዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅ እና በዓለም አቀፍ ስርዓት ውስጥ ውክልና ማግኘት እንዳለባት እና አፍሪካ በታላቅ ኃላፊነት የበኩሏን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ ናት ብለዋል። አፍሪካ ጠንካራ እና ይበልጥ ተአማኒነት ያለው የዓለም ስርዓት እንዲገነባ አበክራ እንደምትሰራም ተናግረዋል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሰላም እና ደህንነት፣ ልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የቴክኖሎጂ እድገት ምላሽ መስጠት እንዳለበት አመልክተዋል። እነዚህ ፈተናዎች ምላሽ እንዲያገኙ ጥልቅ ትብብር፣ ጠንካራ አጋርነት እና ትርጉም ያለው ዓለም አቀፍ ትብብር እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል። ከፊታችን ያለው ኃላፊነት ግልጽ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የዓለም የባለብዙ ወገን ስርዓት ጊዜውን የሚመጥን ለውጥ እንደሚያስፈልገው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ዋና ጸሐፊው ተመድን ከአፍሪካ ጋር ያለው ትብብር እንዲጠናከር እያከናወነ ላለው ስራ አፍሪካውያን ትልቅ ዋጋ ይሰጣሉ ብለዋል። ዛሬ ኢትዮጵያ ይፋ ያደረጋቻቸው ታሪካዊ ቴምብሮች ለተመድ እሳቤዎች ትግበራ ለተጉ በሙሉ እውቅና የሚሰጡ መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የባለብዙ ወገን ትብብር ፍትሃዊ፣ አካታች እና ውጤት ተኮር መሆን እንዳለበት በጽኑ ታምናለች፣ ለዚህ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዓለም መጻኢ ሁኔታ የበኩሏን ሚና እንደምትወጣ ገልጸው አሁን ባለንበት ዓለም ትብብር ለሰላምና መረጋጋት ቁልፍ ምሰሶ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊ ክብር ጋር ተጣጥሞ የተዘጋጀ ነው
May 13, 2026 351
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፡- የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ከኢትዮጵያ ሰላምና ደኅንነት፣ ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊ ክብር ጋር ተጣጥሞ የተዘጋጀ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ ገለጹ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ግብዓት የማሰባሰብ የባለድርሻ አካላት ውይይት አካሂዷል። የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕንባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በሰጡት ማብራሪያ፤ ረቂቅ አዋጁ የህዝብና መንግስትን መተማመን የሚያጎለብት የመረጃ ተደራሽነትን እንደሚያሰፋ ገልጸዋል። የመረጃ ነጻነት ማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ የቴክኖሎጂ ፈጣን ዕድገትና የመረጃ ነፃነትን የበለጠ ለማስፋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። ረቂቅ አዋጁም ለመብትና ነፃነቶች መከበር፣ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ፣ መልካም አስተዳደርና ሙስናን ለመከላከል ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ለውጦች መመዝገባቸውና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድገት ነባሩን አዋጅ ለማሻሻል ገፊ ምክንያቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በረቂቅ አዋጁም መረጃ የማግኘት መብት የሚገደብባቸው ልዩ ሁኔታዎች ከአፍሪካ ሞዴል የመረጃ ነፃነትና ዓለም አቀፍ ሕግጋት ጋር በማጣጣም በግልፅ እንዲቀመጥ መደረጉን አስረድተዋል። መገናኛ ብዙኅን በአጭር ጊዜ መረጃዎችን በማሰባሰብ ለህዝብ በቀላሉ የሚያደርሱበትን የአሰራር ሥርዓት የሚያሳልጥ መሆኑን አብራርተዋል። በረቂቅ አዋጁ ላይ አስተያየት የሰጡት ባለድርሻ አካላትም፤ የመረጃ ነፃነት ከሀገር ብሔራዊ ጥቅምና ደኅንነት ጋር የተገናዘበ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። በዚህም አዋጁ በረቂቅ ደረጃ መሻሻሉ የመረጃ ነፃነትን የበለጠ በማጠናከር የዲጂታል ሚዲያ ምኅዳሩን ተወዳዳሪነት በሚያበረታታ መልኩ መሆኑን ገልጸዋል። ዋና ዕንባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በሰጡት ሃሳብ፤ ባለድርሻ አካላት የሰጧቸው አስተያየቶች የረቂቅ አዋጅ ዝግጅቱን በግብዓት የሚያጎለብቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በረቀቂ አዋጁ ላይ መረጃ ከተቋማት የሚሰጥበት ጊዜ ከ30 ወደ 21 ቀናት ዝቅ የተደረገ ሲሆን፤ አስቸኳይ መረጃም በ48 ሰዓታት እንዲሰጥ መመላከቱን ተናግረዋል። የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጁም ከባለድርሻ አካላት የተሰጡ ግብዓቶችን በማካተት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲቀርብ ይደረጋል ብለዋል። በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ እንዳሉት፤ ረቂቅ አዋጁ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲሰጡና ኢትዮጵያ የደረሰችበትን ደረጃ በሚመጥን መልኩ የተሻሻለ ነው። በቀጣይም ረቂቅ አዋጁን ለማዳበርና ለማጽድቅ ከባለድርሻ አካላት የሚነሱ ግብዓትና ሃሳቦችን በማካተት ለምክር ቤቱ መቅረብ እንደሚኖርበት አሳስበዋል። የመረጃ ነጻነት ከሀገር ሰላምና ደኅንነት፣ ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊ ክብር ጋር ተጣጥሞ የተዘጋጀ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመለሱ
May 13, 2026 313
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፡- የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመልሰዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን ያጠናቀቁትን የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል። ፕሬዚዳንት ማክሮን በቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ የትብብር ጉዳዮች ዙርያ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። የመሪዎቹን ውይይት ተከትሎም ኢትዮጵያና ፈረንሳይ የታዳሽ፣ የተቀናጀና ዘላቂ ኃይል እንዲሁም የዲጂታላይዜሽን ፕሮግራምን ለመተግበር የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት እንዲሁም የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል የመንግሥትና የግል አጋርነት አዲስ የማዕቀፍ እና የፍኖተ ካርታ ልውውጥ አድርገዋል። የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከ125 ዓመታት በላይ ያስቆጠረና በጠንካራ የታሪክ መሰረት ላይ የተገነባ ነው፡፡ ኢትዮጵያና ፈረንሳይ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ግንኙነታቸውን ወደ ልዩ ስትራቴጂካዊ አጋርነትም አሳድገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጥቅምት 2011 ዓ.ም በፈረንሳይ ያደረጉትን ይፋዊ ጉብኝት ተከትሎ፣ የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በአምስት ወራት ውስጥ ኢትዮጵያን መጎብኘታቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡ ፕሬዚዳንት ማክሮን የአሁኑ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሦስተኛው ሲሆን ከዚህ ቀደም በመጋቢት 2011 ዓ.ም እና በታህሳስ 2017 ዓ.ም ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ አውጥታለች
May 13, 2026 235
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ ይፋ ማድረጓን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ ማውጣቷን በመልዕክታቸው ላይ አስፍረዋል። አራቱ ቴምብሮች እ.ኤ.አ. በ1945 በሳንፍራንሲስኮ የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን ከመፈረም ጀምሮ፣ በኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይሎችን እስከ ማሰማራት እና በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደውን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ማስተናገድን ጨምሮ የጋራ ታሪክን የሚተርኩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዓለም የፖስታ ህብረት በኩል ለ192 ሀገራት የተሰራጩት እነዚህ ቴምብሮች፣ ለትውልድ ሁሉ የሚተርፍ የታሪክ ዐሻራ ማሳያ መሆናቸውንም አመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር አድናቆታቸውን ገልጸዋል። የተባበሩት መንግሥታት የጸናው ሀገራት ከመከፋፈል ይልቅ ውይይትን በመምረጣቸው መሆኑን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያም ይህንኑ የሁልጊዜ ምርጫዋን እንደምታጸና አስታውቀዋል።
ፖለቲካ
በጠቅላላ ምርጫው የወጣቶችን ተሳትፎ ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጓል
May 14, 2026 2
ጭሮ /ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በጠቅላላ ምርጫው የወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ወጣቶች ማህበር አስታወቀ። የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እና ለሀገር መፃኢ ዕድል ቁልፍ መሣሪያ ነው። በዞኑ ወጣቶች በምርጫው ሂደት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የምርጫ ካርድ እንዲወስዱ ሰፊ ቅስቀሳ ተደርጓል። የወጣቶችን የምርጫ ተሳትፎ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ወጣቶች በታዛቢነት እና በምርጫ አስፈጻሚነት እንዲሳተፉ በማድረግ የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እየተሰራም ይገኛል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ወጣቶች ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ሙርቴሳ መሐመድ እንደገለፁት፤ በጠቅላላ ምርጫው እውን በሚሆነው የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የወጣቶችን ተሳትፎ ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጓል። ወጣቱ በዕውቀት ላይ ተመስርቶ እንዲመርጥ እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እየተሰጠ ነው ብለዋል። ምርጫ ለሰላምና ለዴሞክራሲ ግንባታ መሰረታዊ ጉዳይ በመሆኑ ወጣቱ በንቃት በመሳተፍ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ለዚህም ማህበሩ ግንዛቤ ከመስጠት ባለፈ፣ በዞኑ በሚገኙ 15 ወረዳዎችና 5 ከተሞች ውስጥ ሂደቱን የሚከታተሉ 2 ሺህ 756 የምርጫ ታዛቢዎችን መድቧል ነው ያሉት። ወጣቱ የአንድ ሰው ድምጽ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለውን ወሳኝነት በመረዳት በካርዱ የሚበጀውን የፖለቲካ ፓርቲ በዕውቀት እንዲመርጥም ጥሪ አቅርበዋል። ከጭሮ ከተማ ወጣቶች መካከል ወጣት አብደላ መሐመድ እና ወጣት መሐመድ ሐሰን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በከተማው ወጣቶች ማህበር በኩል በተፈጠረው ግንዛቤ የምርጫ ካርድ በመውሰድ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል። በምርጫ ካርዳቸው ለሀገር ግንባታ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥም በመገናኛ ብዙሃን እና በተለያዩ አማራጮች የሚደረጉ የምርጫ ቅስቀሳዎችን እየተከታተሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ምርጫው ስኬታማ እንዲሆን የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል
May 14, 2026 74
ደደር፤ ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፡- 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ስኬታማ እንዲሆን የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የደደር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የደደር ከተማ ነዋሪዎች፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልጸዋል። ነዋሪዎቹ ምርጫው ስኬታማ እንዲሆንና ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲከናወን ከሚመለከታቸው የሰላም፣ የቁጥጥርና ሌሎች አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ላይ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አባገዳ አብዱማሊክ ጁንዲ፤ ምርጫው ነፃና ሰላማዊ ሆኖ እንዲካሄድ የላቀ ድርሻና ኃላፊነት እንዳለባቸው በመገንዘብ እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው። ህዝቡ በምርጫው እንዲሳተፍ ለማድረግ ከሁሉም አካላት ጋር በመቀናጀት መስራታቸውን ጠቁመው፤ መራጩ ህዝብም በድምጽ መስጫ ወቅት ይበጀኛል ለሚለው ፓርቲ ድምጹን እንዲሰጥና ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። ምርጫው የዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብት ማረጋገጫ ነው ያሉት ደግሞ በደደር ከተማ በንግድ ስራ የሚተዳደሩት አቶ አብዱሹ አህመድ ናቸው። የመራጮች ምዝገባ መካሄድ ከጀመረበት እለት አንስቶ ህዝቡን የማንቃት ሥራ እየሰሩ መሆኑን አንስተው ምርጫው ያለምንም ችግር ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የበኩሌን እወጣለው ሲሉም አክለዋል። ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ አድናን ሻፊ በበኩላቸው፤ የምርጫውን እለት በጉጉት እየጠበቁና በተለይም ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ምርጫው ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲካሄድ እንዲሁም ወጣቶች በንቃት እንዲሳተፉ የበኩላቸውን ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን የጠቆሙት ደግሞ አቶ አብደላ አህመድ ነው። ለምርጫው ሰላማዊነትና ስኬት በተለይም ወጣቶችን በማስተባበር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
በወሰድነው የመራጭነት ካርድ ለሀገር ልማትና ዕድገት ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
May 14, 2026 72
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የወሰዱትን የመራጭነት ካርድ ለሀገር ልማትና ዕድገት ይበጃል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አስተያየት የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24/2018ዓ.ም መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ። የዘንድሮው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባም ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም የተከናወነ ሲሆን ሁለት የበዓል ቀናትን ሳይጨምር እስከ ሚያዚያ 14/2018 ዓ.ም በማራዘም ተካሂዶ ተጠናቋል። በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ድምፅ መስጫ ካርድ ላልወሰዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች፣ በዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ ተማሪዎችና በካምፕ ለሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በልዩ ሁኔታ እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018ዓ.ም በማራዘም አጠናቋል። መራጮች በዲጂታል "ምርጫዬ" መተግበሪያና በየምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት ከ50 ሚሊየን 514 በላይ መራጮች ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ መውሰድ ችለዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም 47 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን በማስመዝገብ በመገናኛ ብዙኅን አማካኝነት የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ በማስተዋወቅ ላይ ናቸው። በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለምርጫ ታዛቢነት ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር ውስጥ ድርጅቶችም በተለያዩ አካባቢዎች ከ60ሺህ 277 በላይ ወኪሎችን አሰማርተዋል። በመራጮች ትምህርት ላይ ዕውቅና የተሰጣቸው 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ለመራጩ ህዝብ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርትና ስልጠና እየሰጡ ይገኛሉ። በአዲስ አበባ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመመዝገብ ካርድ የወሰዱ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ ለሀገርና ለሕዝብ ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል። ከመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ወርቁ ፍቃዱ እንደገለጹት፤ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ካርድ ከማውጣት ጀምሮ የምርጫውን ቀን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ እየሩሳሌም ሀረገወይን በበኩላቸው፤ በምርጫ ካርዳቸው ለሀገር ልማትና ዕድገት ዕውን መሆን ለሚሰራ ፓርቲ ይሁንታ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ሌሊሳ ጋዲሳም እንዲሁ፤ የምርጫ ካርድ በማውጣት ለሀገር ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የድምፅ መስጫ ቀኑን እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል። የምርጫ ሂደትም ፍትሀዊ፣ ነጻ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። የመዲናዋ ነዋሪ ወደሬ ገብረጻዲቅ እንደተናገሩት፤ ምርጫ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን በመጠቆም፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅት አድርገዋል። አቶ ድሪቢሳ ጥሩነህ በበኩላቸው፤ ምርጫው ሕገ-መንግሥታዊ የመምረጥና መመረጥ ዴሞክራሲያዊ ማረጋገጫ ወሳኝ መድረክ በመሆኑ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገር ሰላም፣ ልማትና ዕድገት መረጋገጥ ለሚሰራ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት ከወዲሁ ተዘጋጅቻለሁ ያሉት ደግሞ አቶ ተሾመ አስፋው ናቸው።
ኢትዮጵያ የባለብዙ ወገን ግንኙነት እና ዓለም አቀፍ ትብብር ተምሳሌት ናት - የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ
May 13, 2026 474
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ትብብርና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ያላትን ቁርጠኝነትና ተምሳሌትነት አደነቁ። ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ አውጥታለች። የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሁነቱን በማዘጋጀታቸውና የኢትዮጵያ ህዝብ ላደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋና አቅርበዋል። ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሩ ለተመድ 80ኛ ዓመት ምስረታ ከመዘከር ባለፈ ተመድ እና ኢትዮጵያ ያላቸውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት የሚያሳይ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1945 ተመድ በሳን ፍራንሲስኮ ሲመሰረት ቻርተሩን ከፈረሙ 51 ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነች አውስተዋል። ኢትዮጵያ አሁን የባለብዙ ወገን እና ዓለም አቀፍ ትብብር ተምሳሌት ሆና መቀጠሏን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔን የምትወክል ሀገር ናት ያሉት ዋና ፀሐፊው በዓለም ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗንም አንስተዋል። እንደ ኢትዮጵያ ጠንካራ የታሪክ መሰረት ያላቸው ሀገራት መጻኢ ጊዜያቸው ጠንካራ እና ብሩህ እንደሆነ ገልጸዋል። አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ ገዢዎች ስር በነበሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ነጻነቷን አስጠብቃ የቆየች ሀገር መሆኗን ገልጸው ይህም የጥንታዊ ስልጣኔዋ ውጤት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነጻ ከወጡ በኋላ የተመድ አባል ሀገራት እንዲሆኑ ድጋፍ ማድረጓንም አስታውሰዋል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀማጫ በአፍሪካ የተመድ ከፍተኛ የተቋማት እና የሰራተኞች ብዛት ከያዙ ከተሞች መካከል እንደምትጠቀስም አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች በተመድ ጥላ ስር በሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ወሳኝ ሚና መጫወታቸውን አንስተውም በዓለም ላይ አደገኛና አስጊ የሚባሉ ቦታዎች በመሄድ መስዋዕትነት በመክፈል ሰላም እና መረጋጋት ለተወጡት ሚና ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ተመድ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ መከባበር መርህ ትብበሩን ማጠናከር እንደሚሻና አጋርነቱን ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆኑን አመልክተዋል። የተመድ ግብ የኢትዮጵያ ህዝብ ማገልገል እና የኢትዮጵያ መንግስት ስትራቴጂዎች እንዲሳኩ መደገፍ ነው ብለዋል። ተመድ ለኢትዮጵያ በሰላምና ደህንነት፣ በልማት፣ በሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት እና የተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ተመድ የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፍትሐዊ የዓለም አስተዳር ስርዓት እንዲሰፍን ያላቸውን ጥሪ እንደሚደግፍና ለስኬታማነቱም እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ማሻሻያ በማድረግ አሁናዊ የዓለም ሁኔታ እንዲያንጸባርቅ እና በአፍሪካ ላይ የደረሱ ታሪካዊ ኢፍትሃዊነቶች መካስ አለባቸው ብለዋል። አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና እንታገኝ በማድረግ የምክር ቤት ቅቡልነት እና ውጤታማነት ማሳደግ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጡም አንስተዋል። አፍሪካ የቅኝ ግዛት እና በዓለም ተቋማት ፍትሃዊ በሆነ ሁኔታ ያለመወከሏ ሁለት ጉዳት መሆኑን ያነሱት ዋና ፀሐፊው ኢትዮጵያ ከተመድ መነሻው የአፍሪካ ተወካይ መሆኗን አድንቀዋል። ተመድ ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሬፎርም እና የአፍሪካ የጸጥታው ምክር ቤት ውክልና እንድታገኝ ያቀረበችው ጥሪ ተገቢና ድርጅቱ ፍላጎቱ እውን እንዲሆን ይሰራል ብለዋል። አፍሪካ በዓለም የፋይናንስ ስርዓት ውስጥ ፍትሐዊ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባትና ውሳኔ ሰጪነቷ ሊያድግ እንደሚገባ አንስተዋል። ኢትዮጵያ ያሳተመችው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ተመድ እስከ አሁን የመጣበትን የሚያወሳ ከመሆን ባለፈ አሁን ዓለም ላይ የታጋረጡ ፈተናዎችን በጋራ መፍታት እንዳለብን የሚያሳስብ ነው ብለዋል። ሰላም፣ ፍትህ እና ብልጽግና ለሁሉም የሚለው የተመድ የጸና እሳቤ ትርጉም ያለው እና የማይተካ መሆኑን አንስተዋል። ለተሻለች አፍሪካ እና ዓለም መፈጠር በጋራ እንስራ ሲሉ ጥሪ ያቀረቡት አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፍትሐዊነት እና የዓለምን አሁናዊ ሁኔታ ያማከለ ለውጥ ያስፈልገዋል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
May 13, 2026 302
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፍትሐዊ፣ አካታች እና የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ያማከለ ለውጥ እንደሚያስፈልገው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ አውጥታለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመርሐ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 80ኛ ዓመት በሚከበርበት ወቅት የባለብዙ ወገን ተቋማት እየተለወጠች ካለው ዓለም ጋር አብረው መጓዝ እንዳለባቸው አጽንኦት መስጠት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል። ከ80 ዓመታት በፊት ከአስከፊው ጦርነት በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መቋቋሙን አውስተዋል። የተመድ መቋቋም ሀገራት በጋራ መርህ ለሰላም፣ ክብር እና መረጋጋት በትብብር መስራት አለባቸው ከሚለው እሳቤ የመነጨ መሆኑን አመልክተዋል። ይህ እሳቤ በተመድ ቻርተር ውስጥ መካተቱን ጠቅሰው ለሰብዓዊ ክብር፣ ፍትህ፣ እኩልነት እና ማህበራዊ ለውጥ የቻርተሩ ምሰሶዎች እንደሆኑ ነው ያነሱት። ኢትዮጵያ ከተመድ መስራች ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዓለም አቀፍ ስርዓት ውስጥ ያላት ታሪክ በመርሕ የተመሰረተ እና ከፍተኛ ፈተናን ያለፈ መሆኑን አመልክተዋል። የጋራ ደህንነት እሳቤ ውጤታማ ባልሆነበት የሊግ ኦፍ ኔሽን ውድቀት ኢትዮጵያ በወቅቱ መመልከቷን ጠቅሰው፤ ያ ታሪክ ኢትዮጵያ ለትብብር ጀርባውን እንዳትሰጥ ማድረጉን ነው ያነሱት። ኢትዮጵያ በወቅቱ ከነበረው ሁነት ትምህርት መውሰዷንና የተቋማት ተአማኒነት የሚለካው በፈተና ወቅት በሚሰጠው ምላሽ መሆኑን የጸና አቋም መያዟን ተናግረዋል። በሀገራት መካከል ያለ መተማመን ጫና ውስጥ ገብቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግጭቶች ይበልጥ እየተወሳሰቡ መምጣታቸውን አንስተዋል። በቃል ኪዳኖች እና በትበራዎች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ መምጣቱንም አስረድተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አሁናዊ የዓለም ሁኔታን ያማከለ፣ ፍትሃዊ እና አካታች በሆነ መልኩ ራሱን እየለወጠ መሄድ እንዳለበትም አስገንዝበዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅ እና በዓለም አቀፍ ስርዓት ውስጥ ውክልና ማግኘት እንዳለባት እና አፍሪካ በታላቅ ኃላፊነት የበኩሏን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ ናት ብለዋል። አፍሪካ ጠንካራ እና ይበልጥ ተአማኒነት ያለው የዓለም ስርዓት እንዲገነባ አበክራ እንደምትሰራም ተናግረዋል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሰላም እና ደህንነት፣ ልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የቴክኖሎጂ እድገት ምላሽ መስጠት እንዳለበት አመልክተዋል። እነዚህ ፈተናዎች ምላሽ እንዲያገኙ ጥልቅ ትብብር፣ ጠንካራ አጋርነት እና ትርጉም ያለው ዓለም አቀፍ ትብብር እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል። ከፊታችን ያለው ኃላፊነት ግልጽ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የዓለም የባለብዙ ወገን ስርዓት ጊዜውን የሚመጥን ለውጥ እንደሚያስፈልገው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ዋና ጸሐፊው ተመድን ከአፍሪካ ጋር ያለው ትብብር እንዲጠናከር እያከናወነ ላለው ስራ አፍሪካውያን ትልቅ ዋጋ ይሰጣሉ ብለዋል። ዛሬ ኢትዮጵያ ይፋ ያደረጋቻቸው ታሪካዊ ቴምብሮች ለተመድ እሳቤዎች ትግበራ ለተጉ በሙሉ እውቅና የሚሰጡ መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የባለብዙ ወገን ትብብር ፍትሃዊ፣ አካታች እና ውጤት ተኮር መሆን እንዳለበት በጽኑ ታምናለች፣ ለዚህ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዓለም መጻኢ ሁኔታ የበኩሏን ሚና እንደምትወጣ ገልጸው አሁን ባለንበት ዓለም ትብብር ለሰላምና መረጋጋት ቁልፍ ምሰሶ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊ ክብር ጋር ተጣጥሞ የተዘጋጀ ነው
May 13, 2026 351
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፡- የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ከኢትዮጵያ ሰላምና ደኅንነት፣ ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊ ክብር ጋር ተጣጥሞ የተዘጋጀ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ ገለጹ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ግብዓት የማሰባሰብ የባለድርሻ አካላት ውይይት አካሂዷል። የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕንባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በሰጡት ማብራሪያ፤ ረቂቅ አዋጁ የህዝብና መንግስትን መተማመን የሚያጎለብት የመረጃ ተደራሽነትን እንደሚያሰፋ ገልጸዋል። የመረጃ ነጻነት ማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ የቴክኖሎጂ ፈጣን ዕድገትና የመረጃ ነፃነትን የበለጠ ለማስፋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። ረቂቅ አዋጁም ለመብትና ነፃነቶች መከበር፣ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ፣ መልካም አስተዳደርና ሙስናን ለመከላከል ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ለውጦች መመዝገባቸውና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድገት ነባሩን አዋጅ ለማሻሻል ገፊ ምክንያቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በረቂቅ አዋጁም መረጃ የማግኘት መብት የሚገደብባቸው ልዩ ሁኔታዎች ከአፍሪካ ሞዴል የመረጃ ነፃነትና ዓለም አቀፍ ሕግጋት ጋር በማጣጣም በግልፅ እንዲቀመጥ መደረጉን አስረድተዋል። መገናኛ ብዙኅን በአጭር ጊዜ መረጃዎችን በማሰባሰብ ለህዝብ በቀላሉ የሚያደርሱበትን የአሰራር ሥርዓት የሚያሳልጥ መሆኑን አብራርተዋል። በረቂቅ አዋጁ ላይ አስተያየት የሰጡት ባለድርሻ አካላትም፤ የመረጃ ነፃነት ከሀገር ብሔራዊ ጥቅምና ደኅንነት ጋር የተገናዘበ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። በዚህም አዋጁ በረቂቅ ደረጃ መሻሻሉ የመረጃ ነፃነትን የበለጠ በማጠናከር የዲጂታል ሚዲያ ምኅዳሩን ተወዳዳሪነት በሚያበረታታ መልኩ መሆኑን ገልጸዋል። ዋና ዕንባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በሰጡት ሃሳብ፤ ባለድርሻ አካላት የሰጧቸው አስተያየቶች የረቂቅ አዋጅ ዝግጅቱን በግብዓት የሚያጎለብቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በረቀቂ አዋጁ ላይ መረጃ ከተቋማት የሚሰጥበት ጊዜ ከ30 ወደ 21 ቀናት ዝቅ የተደረገ ሲሆን፤ አስቸኳይ መረጃም በ48 ሰዓታት እንዲሰጥ መመላከቱን ተናግረዋል። የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጁም ከባለድርሻ አካላት የተሰጡ ግብዓቶችን በማካተት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲቀርብ ይደረጋል ብለዋል። በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ እንዳሉት፤ ረቂቅ አዋጁ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲሰጡና ኢትዮጵያ የደረሰችበትን ደረጃ በሚመጥን መልኩ የተሻሻለ ነው። በቀጣይም ረቂቅ አዋጁን ለማዳበርና ለማጽድቅ ከባለድርሻ አካላት የሚነሱ ግብዓትና ሃሳቦችን በማካተት ለምክር ቤቱ መቅረብ እንደሚኖርበት አሳስበዋል። የመረጃ ነጻነት ከሀገር ሰላምና ደኅንነት፣ ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊ ክብር ጋር ተጣጥሞ የተዘጋጀ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመለሱ
May 13, 2026 313
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፡- የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመልሰዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን ያጠናቀቁትን የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል። ፕሬዚዳንት ማክሮን በቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ የትብብር ጉዳዮች ዙርያ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። የመሪዎቹን ውይይት ተከትሎም ኢትዮጵያና ፈረንሳይ የታዳሽ፣ የተቀናጀና ዘላቂ ኃይል እንዲሁም የዲጂታላይዜሽን ፕሮግራምን ለመተግበር የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት እንዲሁም የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል የመንግሥትና የግል አጋርነት አዲስ የማዕቀፍ እና የፍኖተ ካርታ ልውውጥ አድርገዋል። የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከ125 ዓመታት በላይ ያስቆጠረና በጠንካራ የታሪክ መሰረት ላይ የተገነባ ነው፡፡ ኢትዮጵያና ፈረንሳይ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ግንኙነታቸውን ወደ ልዩ ስትራቴጂካዊ አጋርነትም አሳድገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጥቅምት 2011 ዓ.ም በፈረንሳይ ያደረጉትን ይፋዊ ጉብኝት ተከትሎ፣ የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በአምስት ወራት ውስጥ ኢትዮጵያን መጎብኘታቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡ ፕሬዚዳንት ማክሮን የአሁኑ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሦስተኛው ሲሆን ከዚህ ቀደም በመጋቢት 2011 ዓ.ም እና በታህሳስ 2017 ዓ.ም ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ አውጥታለች
May 13, 2026 235
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ ይፋ ማድረጓን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ ማውጣቷን በመልዕክታቸው ላይ አስፍረዋል። አራቱ ቴምብሮች እ.ኤ.አ. በ1945 በሳንፍራንሲስኮ የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን ከመፈረም ጀምሮ፣ በኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይሎችን እስከ ማሰማራት እና በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደውን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ማስተናገድን ጨምሮ የጋራ ታሪክን የሚተርኩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዓለም የፖስታ ህብረት በኩል ለ192 ሀገራት የተሰራጩት እነዚህ ቴምብሮች፣ ለትውልድ ሁሉ የሚተርፍ የታሪክ ዐሻራ ማሳያ መሆናቸውንም አመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር አድናቆታቸውን ገልጸዋል። የተባበሩት መንግሥታት የጸናው ሀገራት ከመከፋፈል ይልቅ ውይይትን በመምረጣቸው መሆኑን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያም ይህንኑ የሁልጊዜ ምርጫዋን እንደምታጸና አስታውቀዋል።
ማህበራዊ
አዲስ አበባ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን ከከተማ ፕላንና ልማት ጋር በማቀናጀት መተግበሯ በአርዓያነት የሚጠቀስ ነው
May 14, 2026 90
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን ከከተማ ፕላንና ልማት ጋር በማቀናጀት መተግበሯ በአርዓያነት የሚጠቀስ አስደናቂ ተግባር ነው ሲሉ ዓለም አቀፍ ተመራማሪዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎች ግንባታ ለሌሎች የዓለም ከተሞች አርዓያ የሚሆኑ መሆናቸውንም ተናግረዋል። አዲስ ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ “አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ሥርዓት ለውጥ የግንባር ቀደምትነት ሚና፤ ከአካባቢያዊ ሞዴሎች ወደ ዓለምአቀፍ እንቅስቃሴ” በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡ በዚህም ከፅንስ እስከ ስድስት ዓመት የዕድሜ ክልል የሚደረግ ስኬታማ ኢንቨስትመንት አዲስ አበባን የአፍሪካ ተመራጭ የህፃናት ማሳደጊያ ከተማ እያደረጋት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ በአዲስ አባባ እየተከናወነ ያለውን የቀዳማይ ልጅነት ልማት በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት ተመራማሪዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች፤ ከተማዋ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ከከተማ ፕላንና ልማት ጋር አስተሳስራ እየሰራች ያለችበት መንገድ አስደናቂ ነው፡፡ በፈረንሣይ ሬንስ ዩኒቨርሲቲ የወላጆች አዕምሮ ተመራማሪ ጆዲ ፓውሉስኪ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በአዲስ አበባ እየተተገበሩ ያሉ ፈጣን የልማት ስራዎች የከተማ እድገት ለህፃናት ደህንነትና ለጤና አስፈላጊ የሆኑ መሠረታዊ ጉዳዮችን እንዴት ማካተት እንዳለበት የሚያሳይ ትልቅ ምሳሌ ናቸው፡፡ ከተማዋ ደህንነቱ የተጠበቀ አካባቢን፣ አረንጓዴ ቦታዎችንና የመጫወቻ ስፍራዎችን በማስፋፋት በኩል ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለችም ብለዋል። ይህም ለቤተሰቦች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ፣ ሌሎች የዓለም ከተሞችም የአዲስ አበባን ተሞክሮ በመቀመር በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ እነዚህ የልማት ስራዎች ለህፃናት እድገትና ለአጠቃላይ ማህበረሰቡ ጤና የሚኖራቸው ሚና እጅግ አስፈላጊ እንደሆነም ነው የጠቆሙት፡፡ የከተማ ፕላኒንግ እና አርክቴክቸር ፕሮፌሰር የሆኑት አሩናቫ ዳስጉፕታ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አዲስ አበባ ለህፃናት ምቹ የሆኑ ስፍራዎችን ለመፍጠር የሚታዩና ተግባራዊ የሆኑ በርካታ አበረታች እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች ብለዋል፡፡ ከተማዋ እያሳየችው ያለው ጠንካራ ቁርጠኝነት እና የተጀመሩ ተነሳሽነቶች አሁኑኑ በግልጽ በስራ እየታዩ መሆናቸው ለሌሎች የአፍሪካ ከተሞች ትልቅ ተሞክሮ እንደሚሆኑ ገልጸዋል፡፡ የአዲስ አበባ ተሞክሮ ሌሎች የዓለም ከተሞች በፍጥነት ሊቀስሙት የሚገባ ጠንካራ ምሳሌ መሆኑም ጠቅሰዋል፡፡ በሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የህፃናት እድገት ማዕከል ከፍተኛ ባልደረባ የሆኑት ጄምስ ኬርንስ እንዳሉት፤ በአዲስ አበባ የቅድመ ሕፃናት እንክብካቤ ተነሳሽነት ከኮሪደር እና ከአረንጓዴ ልማት ጋር መቀናጀቱ ከተማዋን ለቤተሰብ ምቹ የማድረግ ስትራቴጂ አካል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በከተማው ለሕፃናትና ለቤተሰቦች ደጋፊ የሆነች ከተማን ለመፍጠር በወላጆች አማካሪዎች፣ በሕፃናት ማቆያ ማዕከላትና በመጫወቻ ስፍራዎች ግንባታ ላይ የተመዘገበው እድገት እጅግ አስደናቂ መሆኑ ተናግረዋል፡፡ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ለልጆች እድገት አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶች በጥሩ ሁኔታ እንዲገነቡ መደረጉ ለከተማዋ የልማት ዕቅድ መጠናከር እንደ ጠንካራ ምሰሶ ተጠቃሽ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በተለያዩ ምክንያቶች ከሀገር የወጡ የኢትዮጵያ ቅርሶች በዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንዲመለሱ እየተደረገ ነው
May 14, 2026 127
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በተለያዩ ምክንያቶች ከሀገር የወጡ የኢትዮጵያ ቅርሶች በመንግስት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ገለጹ። በእንግሊዝ ሀገር የነበሩ የኢትዮጵያ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። ቅርሶቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፣ አሉላ ፓንክረስት (ዶ/ር) እና ተተኪ አርበኞች አቀባበል አድርገዋል። ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በተለያዩ ምክንያቶች ከሀገር የተወሰዱና ተዘርፈው የነበሩ የኢትዮጵያ ቅርሶች በመንግስት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንዲመለሱ እየተደረገ ነው። በዛሬው እለትም የአፄ ቴዎድሮስ የእጃቸው የወርቅ አምባር፣ የፀጉራቸው ቁንዳላ (ትንሽ ዘለላ) እና የሸማ ሸሚዝ ቁራጭ ቅርሶች ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን አስረድተዋል። መንግስት ባደረገው ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ጥረትና በተደረገ ስምምነት ቅርሶቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ መደረጉንም ገልጸዋል። ይህም በኢትዮጵያና በእንግሊዝ ተቋማት ትብብር የተገኘ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ውጤት መሆኑን ተናግረዋል። ቅርሶቹን በተዘጋጀላቸው ሙዚየም በክብር በማስቀመጥ ዜጎች ታሪክና ማንነታቸውን እንዲገነዘቡ ይደረጋል ብለዋል። በቀጣይም በተለያዩ ምክንያቶች የተወሰዱ ቅርሶችን ለማስመለስ የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። ማህበራዊ አንትሮፖሎጂስትና ተመራማሪ አሉላ ፓንክረስት (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ቅርሶቹ ከአፄ ቴዎድሮስ ጋር ቁርኝት ያላቸው ናቸው ብለዋል። በእንግሊዝ የኪንግስ ኦን ሮያል ሬጅመንት ሙዚየም ትረስት ሊቀመንበር ሮቢን ጃክሰን (ዶ/ር)፤ ከ150 ዓመታት በኋላ እነዚህን ቅርሶች ወደ ቤታቸው መመለስ መቻሉ ድንቅ አጋጣሚ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ቅርሶች ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ በማድረግ ሂደት በነበራቸው እገዛም ትልቅ ኩራት እንደሚሰማቸው ተናግረዋል።
በህፃናት ላይ በትኩረት መስራት የወደፊት ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መንገድ ነው
May 13, 2026 255
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ በህፃናት ላይ በትኩረት መስራት ድህነትን ለመቅረፍና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መንገድ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ ገለፁ። ላለፉት ሶስት ቀናት “አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ስርዓት ለውጥ የግንባር ቀደምትነት ሚና፤ ከአካባቢያዊ ሞዴሎች ወደ ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ” በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው አዲስ ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባኤ ተጠናቋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ በጉባኤው ማጠናቀቂያ በህፃናት ላይ የሚደረግ መዋዕለ ንዋይ ድህነትን ለመቅረፍና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ቁልፍ መሆኑን ተናግረዋል። ይህ ጉባኤ በዘርፉ ያሉ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች የተለዋወጡበትና ለወደፊት ትብብር መሰረት የጣለ ነው ብለዋል። ከተማዋ እያከናወነችው ያለው የኮሪደር ልማትና ሌሎች የልማት ስራዎች አዲስ አበባን ለህፃናት ተስማሚ እና ለሁሉም ተደራሽ የማድረግ ዓላማን የያዙ መሆናቸው ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ይህንን በየሁለት ዓመቱ በቋሚነት እንደምታዘጋጅ ገልጸው፤ ለጉባኤው ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላደረጉ የአፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል እና ለሌሎች አጋር አካላትን አመስግነዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በበኩላቸው፤ ጉባኤው መንግሥት አጋር ድርጅቶችና ማህበረሰቡ ለጋራ ዓላማ ሲቆሙ ለሕፃናት ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር የታየበት መድረክ ሆኗል ብለዋል። ኢትዮጵያ በዘርፉ ያገኘችውን ውጤታማ ተሞክሮ ወደ ሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ለማስፋፋት መታቀዱንም ገልጸዋል። አፍሪካ ያላትን ሀገር በቀል እውቀትና ተሞክሮ በመጠቀም ዓለም አቀፉን የቀዳማይ ልጅነት እድገት አጀንዳ የመምራት አቅም እንዳላት በጉባኤው አሳይታለች ብለዋል። የአፍሪካ ቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ከበደ ወርቁ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ጉባኤው አህጉራዊ አጋርነትን በማጠናከር ረገድ ትልቅ ስኬት አስመዝግቧል። መድረኩ የአንድ ጊዜ ብቻ ሳይሆን ቋሚ አህጉራዊ የልምድ ልውውጥ ማዕከል ሆኖ እንደሚያገለግልና አፍሪካ በዘርፉ ያላትን ዓለም አቀፍ መሪነት የምታረጋግጥበት እንደሚሆን አመልክተዋል።
በዞኑ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማልማት ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን ለማጉላት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
May 13, 2026 218
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፡-የቱሪስት መዳረሻዎችን በማልማት ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን ለማጉላት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የወላይታ ዞን አስተዳደር ገለጸ። በዞኑ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራዎችን በአንድ የተቀናጀ መዋቅር (Master Plan) በመምራት የአዋጭነት ጥናት እና የሀብት ምዝገባ ማካሄድ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ ማሟላት፣ የማኅበረሰብ ተሳትፎ እና የሰው ኃይል ልማት፣ የሕግ ማዕቀፍ እና የፋይናንስ ሥርዓት ማዘጋጀትና በዘላቂነት በማስተዋወቅ የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ለማጉላት እየተሰራ ነው። የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ እንደገለጹት፣ ዞኑ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራዎችን በማልማትና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን በማጉላት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው። ለዚህም በእያንዳንዱ የከተማና የወረዳ መዋቅር አንድ የመስህብ ስፍራን በማልማት የዘርፉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግም የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አቅም መገንባትና የቱሪስት መዳረሻዎችን ማልማትና ማስተዋወቅ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የዞኑ ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ፀጋ ፋንታ በበኩላቸው እንዳሉት በዞኑ ባሉ መዋቅሮች በእያንዳንዳቸው አንድ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራ ለማልማት በተያዘው ዕቅድ መሰረት ወደተግባር ተገብቶ እየተሰራ ነው። ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ በዞኑ ለቱሪዝም ልማት በተሰጠው ትኩረት ከ100 በላይ ተፈጥሯዊ፣ ታሪካዊ እና ሰው ሰራሽ የቱሪዝም መዳረሻዎች መለየታቸውን ጠቅሰዋል። እነዚህን የቱሪዝም ሀብቶች በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም በየመዋቅሩ አንድ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራ የማልማት ዕቅድ ተይዞ ወደ ተግባር መግባቱን አንስተዋል። ይህም ከዚህ ቀደም ለዘርፉ የተነፈገውን ትኩረት በመቀየር የሀብት ምንጭነት ለማሳደግ ማገዙን ጠቁመዋል። በዚህም በዞኑ የጎብኚዎች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 68 ሺህ 454 ጎብኚዎች አካባቢውን በመጎብኘት ከ493 ሺህ ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል። በዞኑ የአበላ አባያ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ ዋኬ በበኩላቸው በወረዳው ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች መካከል የጡባ ኢኮ ቱሪዝም ሳይት አንዱ ነው። ከዞኑ አስተዳደር ጋር በመተባበር ስፍራውን ለቱሪስቶች ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ የልማት ሥራዎች እንደተጀመሩ ገልጸው፣ መዳረሻውን በማልማት ሥራ ባለሀብቶችም ከ600 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ማዋጣታቸውን ተናግረዋል። በአባላ አባያ ወረዳ ፍልውሃዎችና በርካታ የቱሪዝም መዳረሻዎች እንዳሉት የጠቀሱት አቶ ማቴዎስ፣ አልሚ ባለሀብቶችም በወረዳው መዋዕለንዋያቸውን በማፍሰስ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጠይቀዋል። የዲምቱ ከተማ ከንቲባ አቶ አሻግሬ ዮሐንስ በበኩላቸው ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በከተማው ለሚገኘው ፍልውሃ የመዳረሻ መንገድ፣ የወጣቶች መዝናኛ እና የመዋኛ ገንዳ በማሟላት ለቱሪስቶች ምቹ የማድረግ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። መዳረሻውን ይበልጥ ሳቢና ምቹ በማድረግ የጎብኚዎችን ቁጥር ለመጨመርና ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግም ከዞኑ ጋር በመተባበር የማስፋፊያ ሥራ መጀመሩን አስረድተዋል።
ኢኮኖሚ
በኦሮሚያ ክልል በመኽር እርሻ እስካሁን 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት ታርሷል
May 14, 2026 22
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለ2018/19 የምርት ዘመን በመኽር እርሻ ከታቀደው ውስጥ እስካሁን 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት ታርሶ ለዘር መዘጋጀቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ መንግስት በየዓመቱ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለአፈር ዝግጅት፣ ለግብዓት አቅርቦትና ለቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሀላፊ በሪሶ ፈይሳ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ በክልሉ በዘንድሮ የመኽር እርሻ 11 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች በማልማት 367 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል። ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለግብርና ዘርፉ በተሰጠው ትኩረት ከአርሶ አደሮች ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የዘርፉ አመራርና ባለሙያ እቅድ በማውጣት በውይይት ተጠናክሮ የማሳ ዝግጅት በከፍተኛ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በዘር ለመሸፈን ከታቀደው 11 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታሩ ታርሶ ለዘር መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እስካሁን ከታረሰው መሬት ውስጥም አንድ ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑንም አክለዋል። በክልሉ በአሁኑ ጊዜ የዝናብ ሁኔታው ጥሩ ደረጃ ላይ በመሆኑ በተለይም በምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢዎች በአራቱ የወለጋ ዞኖችና ጅማና ኢሉባቦር ዞኖች ቀድመው የሚደርሱ እንደ በቆሎ፣ በሀረርጌ አካባቢዎች ደግሞ የማሽላ ሰብሎች ዘር መዝራት ተጀምሯል ብለዋል። ከታቀደው ማሳ ከስድስት ሚሊየን ሄክታር መሬት በላይ በትራክተር የሚታረስ መሆኑን አንስተው፣ ልማቱ በኩታ ገጠም እንደሚከናወንም ገልጸዋል። በክልሉ በቂ የግብዓት አቅርቦት መኖሩን ጠቅሰው፣ በአሁኑ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ እና 300 ሺህ ኩንታል የሚሆኑ የተለያዩ አይነት ምርጥ ዘሮች በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች መድረሱን አንስተዋል። በኦሮሚያ ክልል ዘንድሮ ለአጠቃላይ የግብርና ልማቱ 10 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያና ከሁለት ሚሊየን ኩንታል በላይ የተለያዩ ምርጥ ዘሮች ጥቅም ላይ እንደሚውሉም ተናግረዋል።
ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትን በማጎናጸፍ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ የሚገኘው አራዳ ፓርክ
May 14, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ የተገነባው አራዳ ፓርክ የቀድሞ ፒያሳ ገጽታን በመቀየር ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትን በማጎናጸፍ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ የሚገኝ ምቹ የመዝናኛ ስፍራ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ጉብኚዎችና ወጣቶች ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ በጥራትና በፍጥነት የተገነቡ ፓርኮች፣ የኮሪደርና የወንዝ ዳር ልማቶች መዲናዋን ዘመናዊና ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛሉ። አዲሱ አራዳ ፓርክ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ከተደረገ ወዲህ በርካታ ጎብኚዎች ስፍራውን እየጎበኙ ይገኛሉ። ኢዜአ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት በመዲናዋ የተሠሩት የልማት ስራዎች የከተማዋን እድገትና ለውጥ ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል። በአራዳ ፓርክ ጉብኝት ሲያደርጉ ያገኘናቸው አቶ ካሳሁን ሙላት፤ በአዲስ አበባ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ሕፃናትን፣ አዋቂዎችንና ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች ያማከሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህ አስደናቂ ልማት ለአሁኑ ትውልድ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱም ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመው ስኬቶቹ የኅብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። ሌላኛዋ የፓርኩ ጎብኚ ተማሪ ማያ ጆን በበኩሏ፤ በመዲናዋ በመንግሥት የተገነቡ ልዩ ልዩ ፓርኮችን መጎብኘቷን አስታውሳ የአራዳ ፓርክ በዓይነቱ ለየት ያለና ማራኪ ገጽታ የተላበሰ ስፍራ ሆኖ እንዳገኘችው ተናግራለች። እነዚህ የልማት ሥራዎች የመዲናዋን ገጽታ ከመለወጥ ባለፈ ለወጣቱ ትውልድ ምቹና ብሩህ ተስፋ የምታሰንቅ ከተማ ለመፍጠር ያስችላሉ ስትል ገልጻለች። ከሐረር ከተማ የመጡትና ፓርኩን ሲጉበኙ ያገኘናቸው አቶ ማሂር ከማል፤ ስፍራው ከጠበቁት በላይ እጅግ አስደናቂ ገጽታ ተላብሶ እንዳገኙት ተናግረዋል። በተለይም በፓርኩ ውስጥ የተገነቡት ዘመናዊ የእግረኛና የሳይክል መንገዶች፣ ማራኪ መናፈሻዎችና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ለጎብኚዎች ልዩ እርካታ እንደሚሰጡ አብራርተዋል። ከልጆቻቸው ጋር በአራዳ ፓርክ ሲዝናኑ ያገኘናቸው አቶ ከማል ሸሞሎ በበኩላቸው፤ መዲናዋ ቀደም ሲል የነበረባትን የመጫወቻ ስፍራ እጥረት በመቅረፍ ለሕፃናት ምቹ አማራጮችን መፍጠር መቻሏን ገልጸዋል። ይህም ሕፃናት በቂ እና ምቹ የመዝናኛ ስፍራ እንዲያገኙ እና አካላዊና ሥነ-ልቦናዊ እድገታቸው ተስተካክሎ እንዲያድጉ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን የመከላከል ስራው በትኩረት እየተከናወነ ነው
May 14, 2026 109
አዲስ አበባ፣ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ህገወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ግብይትና አቅርቦቱን ስርዓት የማስያዝ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ቅንጅታዊ አሰራሩ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ነው ቢሮው አክሎ ያስታወቀው። በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ በነዳጅ አቅርቦት ላይ የሚታየውን ዓለም አቀፋዊ ጫና ለመቋቋም መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በኦሮሚያ ክልል ሰፊ ስራዎች እየተከናወኑ ነው። በቢሮው የንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ደረጀ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በህዝብ ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጫና ለመቀነስ የነዳጅ ግብይትና አቅርቦቱን ስርዓት የማስያዝ ስራ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በክልሉ የነዳጅ አቅርቦቱ ለታለመለት የልማት ግብ እንዲውል ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ለትልልቅ የልማት ፕሮጀክቶች፣ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች፣ ለግብርና ምርቶች ማመላለሻና ለሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠት የማስተናገድ ተግባሩ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በክልሉ የነዳጅ ስርጭትና ግብይቱን በስርዓት ለመምራት የተቋቋመው የተቀናጀ ግብረ-ኃይል ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን አቶ ዲናኦል ገልጸዋል። በዚህም ከአስተዳደር፣ ከፖሊስ፣ ከዐቃቤ ሕግ፣ ከንግድና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት የተውጣጣ ግብረ-ኃይል ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመቆጣጠርና የንግድ ስርዓቱን ለማሳለጥ እያከናወነ ያለው ተግባር ውጤታማ መሆኑን አስረድተዋል። ግብረ-ኃይሉ አጋጣሚዎችን በመጠቀም በህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውር ላይ የተሰማሩ አካላትን በመከታተል ተገቢውን ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም ባለፉት ሁለት ወራት ብቻ በህገ-ወጥ መንገድ ከማደያ ውጭ ተከማችቶ የተገኘ ከ558 ሺህ 313 ሊትር በላይ ነዳጅ በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን አስታውቀዋል። በቁጥጥር ስር የዋለው ይኸው የነዳጅ ምርት በገንዘብ ሲሰላ ግምቱ 85 ሚሊዮን 846 ሺህ 847 ብር ለመንግስት ገቢ መሆኑን አብራርተዋል። ከህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውሩ ጋር በተያያዘም 256 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በሕግ ሲታይ መቆየቱን ጠቁመዋል። ከእነዚህም መካከል እስካሁን 149 ግለሰቦች እስከ 7 ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ መደረጉን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በተከናወኑ የተቀናጁ የቁጥጥር ስራዎችና በተወሰዱ እርምጃዎች በክልሉ የነዳጅ አቅርቦቱ እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግረዋል። ተግባሩን አጠናክሮ በማስቀጠል ረገድ ነዳጁ ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። ህብረተሰቡ በነዳጅ ዝውውር ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን እንዲሁም በግብርና ምርቶች ላይ የሚታዩ ብልሹ አሰራሮችን በመጠቆም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባም ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
የገጠር ኮሪደር ልማቱ የአርሶ አደሩን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው
May 13, 2026 218
ጎንደር፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል እየተከናወነ ያለው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ በመቀየር ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጥ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ገለጸ። በጎንደር ከተማ አስተዳደር በሳይና ሳቢያ ገጠር ቀበሌ የተገነባው የገጠር ኮሪደር ልማት መንደር ዛሬ ተጎብኝቷል፡፡ በጠቅላላ ምርጫው ብልጽግና ፓርቲን በመወከል በጎንደር ከተማና ዙሪያ ገጠር ቀበሌዎች የሚወዳደሩ እጩዎች ትውውቅና ቅስቀሳ ተካሄዷል። የቢሮው ኃላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በክልሉ እየተከናወነ ያለው የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ በመቀየር ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጥ ነው። በለውጡ ዓመታት መንግስት የአርሶ አደሩን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሚያስችል የግብርና ትራንስፎርሜሽንን በመተግበር ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት ዘመናዊ ግብርናን በማስፋፋትና የአርሶ አደሩን የስራ ባህል ከፍ በማድረግ በኩል አዎንታዊ ሚና እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። በጎንደር ከተማ ገጠር ቀበሌዎች የተተገበረው የገጠር ኮሪደር ልማት ለክልሉ ሞዴል መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን መልካም ተሞክሮ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማስፋት ትኩረት ይደረጋል ብለዋል። ጎንደር በለውጡ ዓመታት ታሪኳንና የቀደመ ገናና ስሟን ሊመጥን የሚችል የልማት ተቋዳሽ ለመሆን በቅታለች ያሉት ደግሞ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው። በከተማዋ በታቀፉ የገጠር ቀበሌዎች የሚኖሩ አርሶ አደሮችን የልማቱ ተጠቃሚ በማድረግ በኩል መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሞዴል የገጠር ኮሪደር መንደሮችን መገንባት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ የገጠር ኮሪደር መንደር ልማት አርሶ አደሩን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማላመድ ወደ አዲስ ህይወት እንዲሸጋገር በር የከፈተ በመሆኑ የልማት ስራውን ወደ ሌሎች የገጠር ቀበሌዎች እንዲሰፋ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ስኬታማ እና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አርሶ አደሩ የድርሻውን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል። የሳቢያ ሳይና ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ሞገስ ተስፋሁን እንዳሉት፤ መንግስት በገጠሩ ክፍል የጀመራቸው የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ የአርሶ አደሩን የስራ ባህልና ተነሳሽነት ያሳደገ ነው፡፡ ልማቱ አርሶ አደሩ የነበረው አኗኗር ከመሰረቱ በመቀየር ምቹና ዘመናዊ ኑሮ እንዲመራ አዲስ ምዕራፍን የከፈተ ተግባር ነው ብለዋል፡፡ መንግስት ግብርናው እንዲዘምን ባደረገው ያልተቆጠበ ድጋፍ አርሶ አደሩ ከራሱ ፍጆታ አልፎ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ እንዲሆን ምቹ ሁኔታ ፈጥሮልናል ያሉት አርሶ አደር ጌትነት ጫቅሉ ናቸው፡፡ የሌማት ትሩፋትና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የአርሶ አደሩን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ ያለ ተግባር መሆኑን ነው ያመለከቱት። ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከመራጮች ምዝገባ ጀምሮ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ጠቁመው የድምጽ መስጫውን ቀኑን በጉጉት እየተጠባበቁ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አሶሳ ዩኒቨርሲቲ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ ነው
May 14, 2026 103
አሶሳ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ ከአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ያገኟቸው የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች በእንስሳት እርባታ ስራቸው የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው በአሶሳ ዞን የኡራ ወረዳ አርሶአደሮች ተናገሩ። የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ማዕከል የተሻሻሉ የፍየል ዝርያዎችን በኡራ ወረዳ ለሚገኙ አርሶአደሮች አሰራጭቷል። ዩኒቨርሲቲው በረጅም ጊዜ ምርምር ያገኛቸውና ለአርሶ አደሮቹ ያሰራጫቸው ፍየሎች በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ መንታ ግልገሎችን የሚወልዱና በሽታን የሚቋቋሙ መሆናቸውም ተገልጿል። ፍየሎቹን የተረከቡት የወረዳው አርሶአደሮች ለኢዜአ እንደሚሉት፤ የእንስሳት ዝርያዎቹ በምርታማነታቸውም ሆነ በሽታን በመቋቋም ረገድ ካሏቸው ጠቀሜታ አንጻር የኑሮ ደረጃቸውን ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ። የተሻሻሉ የፍየል ዝርያ ማግኘታቸው የእንስሳት እርባታ ዘርፍን በሳይንሳዊ መንገድ በማከናወን የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርጋቸውም ተናግረዋል። አርሶአደር ዘካሪያ መርሱቅ እና ዘይነብ መኮነን በአሁኑ ወቅት የሚያረቧቸውን ፍየሎች አስፈላጊውን እንክብካቤ እያደረጉላቸው እንደሆነ ገልፀው ከዩኒቨርሲቲው ያገኟቸው ፍየሎች ደግሞ የእንስሳት እርባታ ስራቸውን በተሻለ መልኩ ለመስራት ዕድል እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል። ለፍየል ዝርያዎቹ አስፈላጊውን ጥበቃ በማድረግና አብዝተው በማርባት ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጸዋል። ሌላው አርሶአደር ሙሐመድ ሳሌ በበኩላቸው፤ ከዩኒቨርሲቲው ባገኙት የተሻሻለ የፍየል ዝርያ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ በስፋት ለመሰማራት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። የእንስሳት መኖ እና መጠለያ በማዘጋጀት ከወዲሁ በእርባታው ዘርፍ ውጤታማ ለመሆን እየሰሩ መሆናቸውንም አብራርተዋል። የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የተሻሻሉ የሰብል እና የእንስሳት ዝርያዎችን ለአርሶአደሩ በማድረስ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ነው ያሉት ደግሞ የኡራ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታጀዲን ሙሐመድ ናቸው። ዩኒቨርሲቲው ከዚህ በፊት በምርምር ያወጣቸው የጤፍ ዝርያ የወረዳውን አርሶአደሮች ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ አሁንም የእንስሳት እርባታ ዘርፍን በማዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ የጀመረው የምርምር ስራ የሚደነቅ ነው ብለዋል። የተሻሻሉ የፍየል ዝርያዎችን የተረከቡ አርሶአደሮች ውጤታማ እንዲሆኑ የወረዳው አስተዳደር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
የግለሰቦችን የግል መረጃ ለታለመለት ዓላማ ብቻ ማዋል የሚያስችል የተጠናከረ የግል ዳታ ጥበቃ እየተከናወነ ነው
May 13, 2026 227
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ተቋማት የግለሰቦችን የግል መረጃ ለታለመለት ዓላማ ብቻ ጥቅም ላይ እንዲያውሉ የሚያስችል የተጠናከረ የግል ዳታ ጥበቃ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ባልቻ ሬባ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 1321/2016 ትግበራና አፈጻጸምን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ባልቻ ሬባ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ተቋሙ በህግ በተሰጠው ሥልጣን መሰረት ለግለሰቦች መረጃ የግል ዳታ ጥበቃ እየተደረገ ነው ብለዋል። በዓለም ላይ እየታየ የመጣው ፈጣን የቴክኖሎጂ ዕድገት ለአዋጁ መውጣት ምክንያት መሆኑን ገልጸው፤ የግል መረጃዎች በአግባቡ ካልተያዙ ላልተፈለገ ዓላማ በመዋል የግለሰቦችን መብት እንዲጣስ ያደርጋል ብለዋል፡፡ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አካል የሆነው የግል ዳታ ጥበቃ ሀገራዊ ፖሊሲ ለመቅረጽና ስትራቴጅ ለመንደፍ ግብዓት ሆኖ እንደሚያገለግል ተናግረዋል። ተቋማትም የግለሰቦችን ዳታ ህጋዊ እና ሃላፊነት በተሞላበት አግባብ መጠቀም እና መጠበቅ እንዳለባቸው ገልጸዋል። የግለሰቦችን መረጃ ከታለመለት ዓላማ ውጭ የሚጠቀሙ ተቋማት ተጠያቂ የሚሆኑበት አሰራር እንዳለ ገልጸው፤ ግለሰቦች የግል ዳታ ጥሰት ሲያጋጥማቸው ለተቆጣጣሪው አካል ሪፖርት የሚያደርጉበት ፖርታል ተዘጋጅቷል ብለዋል። በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሳይበር ደህንነት ከፍተኛ ተንታኝ ቤተልሔም መንግስቱ አየር መንገዱ በግል ዳታ ጥበቃ ዙሪያ የካበተ ልምድ እንዳለው ገልጸዋል። በተቋሙ በየጊዜው በግል ዳታ ጥበቃ ማዕቀፉ ዙሪያ ለሰራተኞቹ ግንዛቤ እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊሲ ዳይሬክተር ሳሙዔል ዓለሙ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ 42 ሚሊዮን ዜጎች ብሔራዊ ድጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። በምዝገባ ወቅት ከግለሰቦች የሚወሰዱ ዳታዎች ለታለመላቸው ዓላማ ብቻ እንዲውሉ ጥበቃ ይደረጋል ብለዋል፡፡ በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የዋና ዳይሬክተር ልዩ አማካሪ ፍቅረ ሥላሴ ጌታቸው በበኩላቸው፤ የግል ዳታ ጥበቃ ለዲጂታል ሽግግር መሰረት መሆኑን አንስተዋል። በግለሰቦችና ተቋማት መካከል መተማመን መፍጠር እንደሚያስችል አብራርተዋል፡፡
የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሳይንስ ሙዚየምን ጎበኙ
May 13, 2026 244
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሳይንስ ሙዚየም ጉብኝት አድርገዋል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በሳይንስ ሙዚየም ያደረጉት ጉብኝት፤ ለሁለቱ ሃገራት የመጪው ዘመን የላቀ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂ እና ከፊት ላሉ ሰፊ ዕድሎች ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ያንጸባረቁበት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጉብኝቱ ተሻጋሪ ርዕይን የሰነቀ አጋርነት፤ ኢትዮጵያና ፈረንሳይ መጻኢ ጉዟቸው ብሩህ መሆኑን የሚያመለክት መሆኑም ተገልጿል።
የኢትዮጵያን የልማት ጉዞ ለማሳለጥ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በምርምር የተደገፉ የፖሊሲ ሀሳቦችን ማቅረቡን ያጠናክራል
May 13, 2026 279
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን የልማት ጉዞ ለማሳለጥ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በምርምር የተደገፉ የፖሊሲ ሀሳቦችን ማቅረቡን ያጠናክራል ሲሉ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፈቃዱ ፀጋ ገለጹ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ "መረጃ ለልህቀት፣ የፖሊሲ ሚና ለበለፀገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሀሳብ የመጀመሪያው የፖሊሲ ቀን መድረክ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሚኒስትሮች በተገኙበት ተካሂዷል። የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፈቃዱ ፀጋ፥ ኢንስቲትዩቱ ሳይንሳዊ ስነ-ዘዴን በመከተልና በማስረጃ ላይ የተመሰረተ ጥናት በማካሄድ፣ የተለያዩ ፖሊሲዎች እንዲወጡ፣ እንዲስተካከሉ ወይም እንዲሻሻሉ የውሳኔ ሃሳቦችን ለመንግስት እያቀረበ ይገኛል ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ስያሜዎች ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው፥ በ2011 ዓ.ም የቀድሞውን የኢትዮጵያ የልማት ምርምር ኢንስቲትዩት (EDRI) እና የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከልን በማዋሃድ እንደ አዲስ መዋቀሩን ገልጸዋል። ይህ አደረጃጀት ሀገራዊ ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀምና የምርምር ትብብርን ለማጠናከር ማስቻሉን ገልጸዋል። ኢንስቲትዩቱ ሀገሪቱ በምታደርገው መዋቅራዊ ሽግግር ነባራዊ ሁኔታዎችንና ህብረተሰባዊ እሴቶችን ያገናዘቡ መፍትሄዎችን በማፍለቅ ረገድ የላቀ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት ከሀገራዊ የልማት አጀንዳዎች አንፃር በ52 የትኩረት የምርምር መስኮች ላይ እየሰራ ይገኛል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፥ በ6 ዋና ዋና የምርምር ማዕከላትና በ14 የፖሊሲ ምርምር ክፍሎች ተዋቅሯል ብለዋል። ባለፉት ስምንት ዓመታት ብቻ ከ320 በላይ የምርምር ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸውንና ከ567 በላይ የምርምር ሪፖርቶች ታትመው ለፖሊሲ ግብዓትነት መብቃታቸውንም አመልክተዋል። በ2020 የግሎባል ጎቱ ቲንክ ታንክ ኢንዴክስ ሪፖርት መሰረት፣ ኢንስቲትዩቱ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት 8ኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን እንደ ትልቅ ስኬት ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከመንግስት፣ ከግል ዘርፍና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የእውቀት ሽግግርና የአቅም ግንባታ ስራዎችን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ኢንስቲትዩቱ እንደ ሀሳብ መፍለቂያ ተቋምነቱ፣ የፖሊሲዎችን ውጤታማነት የመገምገም፣ የተፅዕኖ ምዘና የማካሄድና አዳዲስ የፖሊሲ አማራጮችን ለፖሊሲ አውጭዎች የማቅረብ ኃላፊነቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ስፖርት
ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድን ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከመቀሌ 70 እንደርታ በኢትዮጵያ ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ ይገናኛሉ
May 14, 2026 41
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ድልድል ዛሬ የክለብ ተወካዮች እና የውድድር አመራሮች በተገኙበት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽሕፈት ቤት ወጥቷል። በእጣው መሰረት ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድን ፣ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ መቀሌ 70 እንደርታ የሚጫወቱ ይሆናል። የጨዋታ ቀናት ወደፊት እንደሚገለጽ ፌዴሬሽኑ አስታውቋል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከሀዲያ ሆሳዕና መቻል ከነገሌ አርሲ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
May 14, 2026 79
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 32ኛ ሳምንት ዛሬ በሚደረጉ አራት ጨዋታዎች ይጀመራል። ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡና ከሀዲያ ሆሳዕና በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሲዳማ ቡና በ55 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዟል። ሀዲያ ሆሳዕና በ38 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ከድል የራቀው ሲዳማ ቡና ወደ አሸናፊነት ለመመለስ እና መሪነቱን ለማጠናከር ይፋለማል። በ31ኛ ሳምንት ሃዋሳ ከተማን 1 ለ 0 የረታው ሀዲያ ሆሳዕና ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። በሌላኛው መርሐ ግብር ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ መቻል ከነገሌ አርሲ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታም ትኩረት ስቧል። መቻል በ49 ነጥብ ሶስተኛ፣ ነገሌ አርሲ በ51 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አቻ የወጣው መቻል ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል። ተጋጣሚው ነገሌ አርሲ ተከታታይ የሊግ ድሎችን ያስመዘገበ ሲሆን ሶስት ነጥብ በዋንጫ ፉክክሩ እንዲቆይ ያደርገዋል። በሊጉ አናት ላይ የሚገኙ ክለቦች የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። ወላይታ ድቻ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ያሸነፈው ወላይታ ድቻ በ41 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ተጋጣሚው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ39 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ በ31ኛ ሳምንት መቀሌ 70 እንደርታን 1 ለ 0 አሸንፏል። ሁለቱ ቡድኖች በድል ጉዟቸው ለመቀጠል የሚያደርጉት ጨዋታ ተመጣጣኝ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ምድረ ገነት ሽሬ ከኢትዮጵያ ቡና በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ምድረ ገነት ሽሬ በ33 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ኢትዮጵያ ቡና በ43 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በ31ኛ ሳምንት በአዳማ ከተማ የ4 ለ 0 ሽንፈት ያስተናገደው ምድረገነት ሽሬ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ ቡና ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ሁለቱም የአሸናፊነት መንገድን ለማግኘት ይጫወታሉ። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 32ኛ ሳምንት እስከ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በ14 ጎሎች እየመራ ነው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጫዋቾች የሆኑት አዲስ ግደይ እና ናትናኤል ዳንኤል በተመሳሳይ 10 ግቦች ይከተላሉ።
ኢንተር ሚላን በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ዋንጫውን አነሳ
May 14, 2026 82
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፦ በጣልያን የጥሎ ማለፍ ዋንጫ (ኮፓ ኢጣሊያ) የፍጻሜ ጨዋታ ኢንተር ሚላን ላዚዮን 2 ለ 0 አሸንፏል። ትናንት ማምሻውን በስታዲዮ ኦሎምፒኮ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ላውታሮ ማርቲኔዝ እና የላዚዮው ተከላካይ አዳም ማሩሲች በራሱ ላይ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ውጤቱን ተከትሎ ኢንተር ሚላን ለ10ኛ ጊዜ የጥሎ ማለፉን ዋንጫ አንስቷል። በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ዋንጫውን አስገብቷል። ኢንተር ባለፈው ሳምንት የሴሪአውን ዋንጫ ለ21ኛ ጊዜ ማንሳቱ የሚታወስ ነው። የዛሬው የፍጻሜ ተፋላሚ ላዚዮ የጥሎ ማለፉን ዋንጫን ከሰባት ዓመታት በኋላ የማንሳት ህልሙ አልተሳካም። የሮሙ ክለብ የኮፓ ኢጣሊያን ሰባት ጊዜ አሸንፏል።
ፒኤስጂ የፈረንሳይ ሊግ ዋን አሸናፊ መሆኑን አረጋገጠ
May 14, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018 (ኢዜአ)፦ በፈረንሳይ ሊግ ዋን የ29ኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሐ ግብር ፒኤስጂ ሌንስን 2 ለ 0 አሸንፏል። ትናንት ማምሻውን በቦላሬት- ዴሌሊስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ክቪቻ ክቫራትስኬሊያ እና ኢብራሂም ምባዬ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። በውድድር ዓመቱ ለ24ኛ ጊዜ ድል የቀናው ፒኤስጂ በ76 ነጥብ አንድ ጨዋታ እየቀረው የሊጉ አሸናፊ መሆኑን አረጋግጧል። የሊጉን ዋንጫ ሲያነሳ የአሁኑ ለ14ኛ ጊዜ ነው። ፒኤስጂ ካለፉት 13 የሊግ ዋንጫዎች 11ዱን በማንሳት ፍጹም የበላይነቱን ይዟል። በሊጉ ስምንተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሌንስ በ67 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ሌንስ ዋንጫውን ለማንሳት ያደረገው ብርቱ ፉክክር አድናቆት አስችሮታል።
አካባቢ ጥበቃ
ማዕከሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በማላመድ በግብርና ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ እያገዘ ነው
May 13, 2026 205
ጂንካ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፡-የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በማላመድ በግብርና ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ማገዙን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ ገለጹ። የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲና ሌሎች አመራሮች የማዕከሉን የሥራ እንቅስቃሴ ዛሬ ጎብኝተዋል። በዚህ ወቅት አፈ ጉባኤው እንዳሉት፣ የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል የአርሶና የአርብቶ አደሩን ችግር የሚፈቱና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በማላመድ በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው። ማዕከሉ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው የጥናትና ምርምር ሥራ በክልሉ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ እየተደረገ ላለው ጥረት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ገልጸዋል። ማዕከሉ ያፈለቃቸውን የግብርና ቴክኖሎጂዎች ወደ አርሶና አርብቶ አደሩ በማውረድ ግብርናውን ለማዘመንና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትንም አጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል። የምክር ቤቱ ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ወላይቴ ቢቶ በበኩላቸው፣ የምርምር ማዕከሉ ተግባር በተለይም በቆላማ አካባቢዎች በመስኖ ልማት የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እና የምግብ ዋስትናውን ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚያግዝ ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት በቆላማ አካባቢዎች በመስኖ ልማት የመጣውን ተጨባጭ ለውጥ በማስፋት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት ማዕከሉ የጀመረውን እገዛ ሊያጠናክር ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዮት ሙላቴ (ዶ/ር) የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ በግብርና ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት እንዲመዘገብ እያገዘ መሆኑን አንስተዋል። በክልሉ ቀደም ሲል በሰብል ልማት በሄክታር ከ30 ኩንታል ያነሰ ምርት ይገኝ እንደነበር አስታውሰው፣ የምርምር ማዕከላት የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ማላመዳቸውን ተከትሎ በሄክታር ከ40 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘት ተችሏል ብለዋል። ለውጤቱ በአነስተኛ ቦታ ብዙ ምርት ማግኘት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ማድረግ መቻሉ ሌላው ምክንያት መሆኑንም ጠቅስዋል። እንደ አብዮት (ዶ/ር) ገለጻ፣ ማዕከሉ የሩዝ ምርት ባልተለመደባቸው አካባቢዎች ጭምር የሩዝ ልማትን በማላመድና በማስፋፋት ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል። የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተርና የሰብል ተመራማሪ ተክሌ ዮሴፍ (ዶ/ር) በበኩላቸው የምርምር ማዕከሉ የተጣለበትን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከማዕከሉ የሚወጡ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችና የምርምር ውጤቶችን በአርሶና አርብቶ አደሩ ማሳ በማስፋት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደተቻለም አመልክተዋል። ማዕከሉ በተለይም በዝናብ አጠር አካባቢዎች በመስኖ የሚለሙ እና ምርትን በእጥፍ የሚያሳድጉ የሰብል ዝርያዎችን እያላመደ መሆኑን ጠቁመው፣ ይህም በአርብቶ አደሩ አካባቢ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለውን ጥረት ያግዛል ብለዋል ።
ዩኒቨርሲቲው ሳይንሳዊ የብዝሃ ደን ልማት ስራን የሚደግፍ የዘር ባንክ ሊያቋቁም ነው
May 12, 2026 333
ጎንደር፤ ግንቦት 4/2018 (ኢዜአ)፡- ጎንደር ዩንቨርሲቲ ሳይንሳዊ የብዝሃ ደን ልማት ስራን የሚደግፍ ሀገር በቀል የደን ዛፎች የዘር ባንክ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። በዩኒቨርሲቲው የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ የደን ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ አስማማው ዓለሙ (ዶ/ር) እንደገለጹት የሚቋቋመው የዘር ባንክ የሚስተዋለውን የደን ዘር ጥራትና አቅርቦት ችግር የሚፈታ ነው። የዘር ባንኩ መቋቋም ችግኞች ለአካባቢው ስነ ምህዳር ተስማሚነታቸውን በምርምር በማረጋገጥ የጽድቀት መጠናቸውን ለማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን አመላክተዋል። በተጨማሪም በሽታን፣ ተባይንና ድርቅን በመቋቋም ከአካባቢው ጋር በፍጥነት ተላምደው ውጤታማ መሆን የሚችሉ የደን ዛፍ ዝርያዎችን ለማቆየት የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። የዘር ባንኩ በምርምር ጣቢያዎች ተሞክረውና የጥራት ደረጃቸው በቤተ -ሙከራ ተፈትሾ ያለፉ የደን ዛፍ ዘሮችን በሳይንሳዊ መንገድ ጠብቆ ለማቆየት አጋዥ ሚና ይጫወታል ሲሉም አክለዋል። በዚህም የሀበሻ ጽድ፣ የኮሶ ዛፍ፣ ዋንዛ፣ ወይራና የአካሽያ ግራር የመሳሰሉ የደን ዛፎችን በሳይንሳዊ መንገድ በመንከባከብ ዘር የመሰብሰብ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። እስካሁን በተሰራው ስራም 13 አይነት የዛፍ ዝርያዎችን በማላመድ በአሁኑ ወቅት 254 ኪሎ ግራም ዘር በከተማዋ በተቋቋሙ የችግኝ ጣቢያዎች እንዲፈሉ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል። በተጨማሪም በከተሞች የኮሪደር ልማት የአረንጓዴ የጥላ ዛፍ ችግኞችን ለማቅረብ የሚያስችል ሰርቶ ማሳያ በማቋቋም ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡ በአካባቢው ጥራት ያለው ዘር አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ ባለመኖሩ ለደን ልማት ስራው እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ካህሌ ጀንበር (ዶ/ር) ናቸው፡፡ የዘር ባንኩ መቋቋም እንደ ሀገር እየተካሄደ የሚገኘውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬታማና ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል
May 11, 2026 419
አዲስ አበባ፤ግንቦት 3/2018 (ኢዜአ)፡-73ኛው የታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ትንበያ ፎረም (GHACOF 73) ግንቦት 10 እና 11 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል። ፎረሙ የሚካሄደው “የአየር ንብረት አገልግሎቶች፤ ለአይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና የመተግበሪያ ማዕከል(ICPAC) ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን ፎረሙን እንዳዘጋጀው ተገልጿል። ስብሰባው ትንበያ ከመስጠት ባለፈ ትንበያዎቹን ወደ ተግባር መቀየር እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የቅድመ ማስጠንቀቂያና ቅድመ ዝግጅት እርምጃዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። የአየር ንብረት መረጃዎች አርሶ አደሮች ፣ የጤና ባለሙያዎችን እና የአደጋ ስጋት አመራሮችን በቀጥታ እንዲደግፉ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። በብሔራዊ የሚቲዎሮሎጂ ተቋማት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር ሌላኛው የመወያያ አጀንዳ ነው። መድረኩ ለታላቁ የአፍሪካ ቀንድ ግብርና እና የውሃ ሀብት ወሳኝ የሆነውን ከእ.አ.አ ከጁን እስከ ሴፕቴምበር 2026 ያለውን የዝናብ ወቅት ትንበያ ይቀርብበታል። ሚኒስትሮች፣ የምርምር ተቋማት፣ ሰብአዊ ድርጅቶች፣ የሲቪክ ማህበራት እና የግል ባለሀብቶች ይሳተፋሉ።ይህ የተሳታፊዎች ስብጥር ሳይንስን ከፖሊሲ ጋር ለማገናኘት የታለመ ነው። የአየር ንብረት መዛባት የሩቅ ስጋት መሆኑ ቀርቶ በደጃፋችን ላይ ያለ ተጨባጭ አደጋ ነው ያለው ኢጋድ ፎረሙ በታላቁ የአፍሪካ ቀንድ የሚገኙ ማህበረሰቦች በቂ መረጃ እንዲኖራቸውና አስቀድመው ዝግጁ እንዲሆኑ ማስቻል ላይ ትኩረቱን ያደረገ መሆኑን አመልክቷል።
የኢትዮጵያ የተፋሰስና የአካባቢ ጥበቃ ስኬታማ የልማት መርሃ ግብሮች የበለፀገ የደን ሃብት እንዲፈጠር እያደረገ ነው
May 9, 2026 506
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የተፋሰስና የአካባቢ ጥበቃ ስኬታማ የልማት መርሃ ግብሮች የበለፀገ የደን ሃብት እንዲፈጠር እያደረገ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። በተያዘው በጀት ዓመት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት መርሃ ግብር 3 ነጥብ 9 ሚሊየን ሄክታር መሬት መልማቱንም አስታውቋል። በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ሥራ አስፈፃሚ ፋኖሴ መኮንን፤ የሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋ የፈጠረው የደን መመናመን ከፍተኛ የአካባቢ መራቆትን አስከትሎ ነበር ብለዋል። ይህም የኢትዮጵያ የአፈር ለምነትን በመቀነስ በግብርና ምርታማነት፣ በዱር እንስሳትና ዕፅዋት ደኅንነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል። በዚህም በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ ማግስት በአረንጓዴ አሻራና የአካባቢ ጥበቃ ልማት መርሃ ግብር የሥነ-ምኅዳር ደኅንነት እንዲያገግም ያስቻለ ስኬታማ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በተለይም በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ የህብረተሰቡን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትን ባህል በማጎልበት የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን እያስጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል። በዘንድሮ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመትም በ22ሺህ 59 ተፋሰሶች 4 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለማልማት በተያዘው ዕቅድ፤ እስካሁን 3 ነጥብ 9 ሚሊየን ሄክታር መሬት በበጋ ተፋሰስ መልማቱን አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅትም በተለያዩ ክልሎች የሥነ-ምኅዳር ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ የተፋሰስና የአካባቢ ጥበቃ የልማት ሥራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። ባለፉት ዓመታት በህብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ ሰፋፊ የአፈርና ውሃ ጥበቃ የልማት ሥራዎችም የተራቆተ የመሬት ገፅታ እንዲያገግም በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን አስረድተዋል። የህብረተሰቡ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ባህል እያደገ መምጣቱም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነትም በርካታ ዜጎች በንብ ማነብ፣ እንስሳት መኖ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት መርሃ ግብሮች ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኝ አንስተዋል። ይህም የህብረተሰቡን የአካባቢ ጥበቃ ባለቤትነትን በማረጋገጥ ኢትዮጵያ በደን ሀብት የበለጸገች ለምለም ሀገር እንድትሆን እያደረጋት መሆኑን አንስተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 201
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 254
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 180
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በአዲስ አበባ ይካሄዳል
May 13, 2026 223
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በሕብረቱ ዋና መቀመጫ ዛሬ በአዲስ አበባ ይደረጋል። በውይይቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እንደሚገኙ ይጠበቃል። ውይይቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል በአፍሪካ ልማት እና በዓለም አቀፍ አስተዳደር ዙሪያ ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ቅንጅት፣ የጋራ ተጠያቂነት እና ትብብርን በልማት፣ በአስተዳደር፣ በሰብአዊ ድጋፍ እና በሰላም ግንባታ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ያላቸውን ትስስር ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ይካሄዳል። በዚህ የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ላይ በርካታ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች የሚዳሰሱ ሲሆን፣ በተለይም የአጀንዳ 2063 እና የሁለተኛው የአስር ዓመት ምዕራፍ የትግበራ ዕቅድ አፈፃፀምን ማፋጠን እንዲሁም አፍሪካን በዓለም አቀፍ ፖሊሲ እና አስተዳደር ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና መጠበቅ በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ትኩረት ያደርጋል። በተጨማሪም "ከጥገኝነት ወደ ሉዓላዊነት" የተሸጋገረ የልማት ፋይናንስ፣ የ2026 የአፍሪካ ሕብረት የዓመቱ መሪ ቃል የሆነው ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና የንጽህና አጠባበቅ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ተቋማት ሪፎርም እና አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ያላትን ውክልና የተመለከቱ ጉዳዮች ውይይት ይደረግባቸዋል። መድረኩ ለአህጉራዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔዎችን ማምጣት፣ የአገር ውስጥ ሀብት ማሰባሰብን ማሳደግ፣ የወጣቶች እና የሴቶች ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንዲሁም በአህጉራዊ እና በዓለም አቀፍ የልማት የቅድሚያ ትኩረቶች መካከል ያለውን ትስስር ማጠናከር ወሳኝ መሆኑ አጽንኦት የሚሰጥበት እንደሆነ ተመላክቷል። ከውይይቱ ከሚጠበቁ ውጤቶች መካከል የተሻለ ስትራቴጂካዊ ቅንጅት፣ ፍትሐዊ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ለውጥ፣ በአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ቃል ዙሪያ ጠንካራ ቅንጅት መፍጠር እና በተባበሩት መንግሥታት ሥርዓት ውስጥ ፍትሐዊ የአፍሪካ ውክልና እንዲኖር የቀረቡ ጥሪዎችን ማጠናከር እንደሚገኙበት ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የውይይቱን ውጤቶች አስመልክቶ የጋራ መግለጫ ይሰጣሉ።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 583
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 664
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች
May 3, 2026 743
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር እያሸጋገራት ይገኛል።የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የመሰረተ ልማት እና የተቋማት ግንባታ ስራዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋንኛ ስራዎች ናቸው። ለውጡን ተከትሎ መንግስት "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን ስትራቴጂ በመቅረጽ የዲጂታላይዜሽን ስራውን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሰሶ አድርጎታል። የለውጡ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ ቴክኖሎጂን እንደ አንድ የኢኮኖሚ ምሰሶ በመቁጠር "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን አጠቃላይ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ተግባር ገባ።ይህ ስትራቴጂ የሀገሪቱን የዲጂታል ጉዞ ከመሰረቱ የለወጠ ሲሆን፣የመጀመሪያው ትልቅ እርምጃም የቴሌኮም ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ነበር። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን የማዘመን ስራ የኢንተርኔት ተደራሽነት እንዲሰፋ ምክንያት ሆኗል።በተለይም የአምስተኛ ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን አስችሏታል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ለውጡ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ ውጤት አምጥቷል።እንደ ቴሌብር (telebirr) ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ምንም የባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ፣ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር ትልቅ መደላድል ፈጥረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የተመዘገቡት ስኬቶችም የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ አድማስ ይበልጥ አስፍተውታል። የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያላትን ራዕይ ለዓለም ያሳየችበት አጋጣሚ ነው።ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በጤናው ዘርፍ የካንሰር ህመምንና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ መለየት የሚያስችሉ የኤአይ ውጤቶችን አበልጽጓል። በግብርናውም ረገድ የአፈርን ለምነትና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ዋስትና ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል ዓለም ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱና ለተጠቃሚው ምቹ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የፋይዳ (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን መረጃ በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ፣ ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የለውጡ ፍሬያማነት ማሳያ ነው።የሳይንስ ሙዚየምም የወጣቶችን የፈጠራ አቅም የሚያሳይና የሀገሪቱን ቴክኖሎጂ የሚደግፍ ትልቅ አቅም ሆኗል።የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቅርቡ መጠናቀቁ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2025 ስትራቴጂው መጠናቀቁን ተከትሎ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል።ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዲጂታል 2030ን ይፋ ሲያደርጉ የነበረው ትልቁ መልዕክት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዓለም ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊና መሪ ትሆናለች የሚል ነው። ስትራቴጂው በዋናነት"የፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጋር በማቀናጀት፣ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን መፍጠር፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ስራ እድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት እና ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) አድርጎ መገንባትን እንደ ዋነኛ ግብ አስቀምጧል። ይህም ሁሉን አቀፍ የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ የመንግስት አገልግሎቶችን መቶ በመቶ ወረቀት አልባ በማድረግ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) በግብርና፣ በጤናና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ በስፋት በመተግበር የምርታማነት አብዮት መፍጠርን ያለመ ነው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸው ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችው ስራ በአህጉራዊ ደረጃ ያለውን ተቀባይነትና የተሰጣትን ትልቅ ኃላፊነት የሚያሳይ ነው።ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት የቴክኖሎጂ ከፍታ፣ ሀገሪቱን በአፍሪካ የቴክኖሎጂ ተፎካካሪ ብቻ ሳይሆን የፈጠራ ምንጭ እንድትሆንም እያደረጋት ይገኛል። በዚህ ረገድም የቀጣዩ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ስኬትም ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና በቴክኖሎጂ የበለጸገች ሀገር የማድረግ ራዕይን ለማሳካት እና ለሀገራዊ ብልጽግና እንደ ቁልፍ ሞተር ሆኖ ያገለግላል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 3, 2026 611
ክልሎች፤ሚያዝያ 25/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮች በወፍ በረር ሲቃኙ ይህንን ይመስላሉ!!! 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነቡትን የቶዮ ሶላር ኢነርጂ ምዕራፍ ሁለት፣ የኦሪጂን እና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎችን እንዲሁም የኤች.ዜድ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካን በይፋ መርቀዋል። እነዚህ የሶላር ፋብሪካዎች በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹሕ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን፣ የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካ ደግሞ በዓመት 900 ቶን ኦክስጅን፣ 40,000 ቶን ናይትሮጅን እና 7 ቶን ሃይድሮጅን ለገበያ ያቀርባል። ይህ ክንውን የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ለማፋጠን፣ የኢነርጂ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ዘላቂ፣ የማይበገር ሁለንተናዊ እድገት ዕውን ለማድረግ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል። 👉እንቁላልን ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት የማቆየት ልምምድ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ፤ የዶሮ እንቁላል ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት ያህል ማቆየት የሚያስችል ቴክኖሎጂን ወደ ተግባር ለማስገባት ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል። በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ሕክምናና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ማስተዋል ብርሃን፤ ዩኒቨርሲቲው የእንቁላል ምርት ብክነትና ብልሽትን ለማስቀረት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። በዚህም እንቁላልን እስከ ሁለት ዓመት ያለ ምንም ብልሽት ማቆየት የሚያስችለውን ቴክኖሎጂን የማላመድና የማስተዋወቅ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ቴክኖሎጂው በአንድ ሊትር ውሃ ውስጥ 30 ግራም የኖራ አፈር ወይም ላይም ስቶን ጨምሮ በማዋሃድ እስከ 12 እንቁላሎችን ሳይበላሽ የሚያስቀምጥ በመሆኑ ለአርሶ አደሩ ተመራጭ ነው ያሉት። ይህም እስካሁን ባለው አንድ ትኩስ እንቁላል ሳይበላሽ መቆየት የሚችለው እስከ ሁለት ሳምንት መሆኑን ጠቁመው ቴክኖሎጂው ይሄን ችግር በመሰረታዊነት የሚቀይር ነው።፡ ቴክኖሎጂውን በስፋት በማስተዋወቅና በማላመድ ረገድም ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን በመስጠት ችግር ፈቺነቱን የማሳየት ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። 👉የአፋር ጥጥ ተስፋ ሰጪ ፀጋ! የአፋር ክልል የበርካታ የተፈጥሮ ፀጋዎች ባለቤት ነው፤ ሆኖም እነዚህን እምቅ ሀብቶች ወደ ልማት በመቀየር ከፀጋዎቹ ተቋዳሽ ለመሆን ሳይቻል ለረጅም ተቆይቷል። አሁን ግን ከፀጋዎቹ አንዱ የሆነውን ተፈጥሯዊ ጥጥ (Organic Cotton) ለማምረት ተስፋ ሰጪ ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በሰመራ በተካሄደ የውይይት መድረክም በግብርና ሚኒስቴር የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳምሶን አሰፋ፤ የአፋር ክልል ጥጥን በመስኖ ማልማት የሚቻልበት አቅም ያለው በመሆኑ ልማቱን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። በሀገራችን የጥጥ ልማትን ለማስፋፋት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው፤ ባለፈው የምርት ዘመን እንደ ሀገር በስድስት ክልሎች 110 ሺህ ሄክታር መሬት በጥጥ መልማቱን ተናግረዋል።በዚህም 79 ሺህ ሜትሮክ ቶን የተዳመጠ ጥጥ በማምረት ለኢንደስትሪዎች ማቅረብ እንደተቻለ ነው የገለፁት። 👉የሸማቹ ሸክም ይቀላል! የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን “ወደ ቀበሌ መድረስ” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ስድስት ከተሞች ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ማህበራት ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ ሲያካሄድ የህብረት ስራ ማህበራት ከእንግዲህ የሸማቹን ሸክም ሊያቀሉ ይገባል የሚል ሀሳብ ተነስቷል። በሀዋሳው በተካሔደው የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ላይ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት በተለያዩ መስኮች የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊት ሀገር ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን አንስተዋል። በተከናወኑ ተግባራትም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን አክለዋል። የመንግስትን፣ የግሉ ዘርፍንና የዜጎችን የካፒታል አቅምና ዕውቀትን ደምረው የያዙት የህብረት ስራ ማህበራት ግብርናውን በማሻገር የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት በመቀየር ረገድ ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልፀው የፋይናንስ አቅርቦት ችግርን በመፍታትና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር የሸማቹን ህብረተሰብ ሸክም ያቀላሉ ተብሎ እንደሚታመንም አስረድተዋል። 👉ምርምር ለቀጣናዊ ትስስር በጅማ ዩኒቨርሲቲ "ቀጠናዊ ሰላምና ትብብር ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ባለችበት ቀጣና የሚታዩ ፍላጎቶችን ለማሟላትና ተግዳሮቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለመፍታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ጥናቶች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ ተነስቷል። በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጦሽኔ ቀጣናውን በልማት ለማስተሳሰር በሚደረግ ጥረት የትምህርት ተቋማቱ የጥናትና ምርምር ድጋፍ ከፍተኛ ሚና አለው ያሉ ሲሆን ለዚህም ተቋማቱ ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያሳድጉ እና ማህበራዊ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚያግዙ የፖሊሲ መነሻ ሀሳቦችን በጥናትና ምርምር እንዲያፈልቁ አሳስበዋል። የሚወጡ ጥናቶች በቀጣናው በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ እየተከሰቱ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሊሆኑ እንደሚገባ የተጠቀሰ ሲሆን ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን በመተግበር እያከናወነች ያለችው ተግባር በተመክሮነት ቀርቦ አድናቆትን አስገኝቶላታል። 👉ሻይ ቅጠል አሁን አሁን አርሶ አደሩ በተለያዩ ኢንሼቲቮች በሚከናወኑ የግብርና ልማት ትግበራዎች ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ ይገኛል። በርካታ አርሶ አደሮች በሻይ ቅጠል ልማት ኢንሼቲቭ በመሰማራት ገቢን ከማሳደግ ባለፈ ለሌሎችም ሰፊ የስራ ዕድል እየፈጠሩ ይገኛሉ። በጅማ ዞን የሻይ ቅጠል ልማትን ከማስፋፋት ባለፈ የበያ ትስስር የመፍጠርና ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለፋብሪካ ለማቅረብ ለአርሶ አደሩ ግንዛቤ እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል። የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም፤ በዞኑ የሻይ ቅጠል ልማትን በኢኒሼቲቨን መልክ በመተግበር የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድል እየተፈጠረ ነው። ዘንድሮም ስራውን ለማስቀጠል በተመረጡ 6 ወረዳዎች በመጪው ክረምት የሚተከሉ 50 ሚሊዮን ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን ህዝብን በማሳተፍም ወደ 2 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬትን ለመሸፈንም ታስቧል። ጥቅሙ የገባቸው አርሶ አደሮችም የሰብል ልማቱን ለጊዜው ተወት በማድረግ በሻይ ቅጠል ልማት ላይ እየተሳተፉ እንደሆነ ይናገራሉ። በዞኑ የሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ አርሶ አደር ሲራጅ ሼክ ከድር በሻይ ቅጠል ልማት ላይ መሳተፍ ከጀመሩ ወዲህ ገቢያቸው መጨመሩን ተናግረዋል። አርሶ አደር ሱልጣን አባሞጋ በበኩላቸው ተሰማርተውበት ከነበረው የሰብል ልማት ወደ ሻይ ቅጠል ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። የአካባቢ ፀጋን ተገንዝቦ ወደ ስራ መግባት ተጠቃሚነትን እንደሚያመጣ ማሳያ ሊሆን ይችላል። 👉ተስፋዎች ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በሆሳዕና ከተማ የተካሄደው የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ደረጃ ሽግግር እውቅና መርሃ ግብር ይጠቀሳል። "የኢንተርፕራይዞች ሽግግር ለእመርታዊ እድገት" በሚል መሪ ሀሳብ የተከናወነው የዕውቅና መድረክ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት ነው የተካሄደው። እሳቸው እንደገለፁት፤ ኢንተርፕራይዞቹ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠሩ ነው። በክልሉ በገጠርና በከተማ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ ከ25 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች በተለያዩ መስኮች መሰማራታቸው የተገለፀ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በጥቃቅንና በአነስተኛ ደረጃ የሚገኙ 4 ሺህ 948 ኢንተርፕራይዞችን የማሸጋገርና 495 ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን የመለየት ስራ መሰራቱም እንዲሁ። ከኢንተርፕራይዝ ወደ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሸጋገሩ አምራቾች እንደተናገሩት ሽግግሩ ስራቸውን በተሻለ ሁኔታ ለመከወን እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል። 👉ትምህርትና አርብቶ አደሩ የወፍ በረር ቅኝታችንን ስንቀጥል ጋምቤላ እንደርሳለን፤ በሳምንቱ በጋምቤላ ከተማ በተካሄደ መድረክም የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውም ተመልክቷል። በለውጡ ዓመታት የአርብቶ አደሩን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ውጤት መመዝገባቸውም እንዲሁ። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም ረገድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና የገዘፈ መሆኑም በመድረኩ መገለፁን ቅኝታችን ዳሶታል። 👉ልወቅሽ ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ጠቅለል አድርጎ የዳሰሰው ቅኝታችን ደግሞ በስድስት ከተሞች ለማካሄድ ዕቅድ የተያዘለትና እስካሁን በጅማ፣ በሀዋሳና በደብረ ብርሃን ከተሞች የተካሄደው የ"ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ታላቁ ሩጫ" ከተሞቹን ከማስተዋወቅ የዘለለ ፋይዳውን በመርሃ ግብሩ ላይ በተላለፉ መልዕክቶቹ አሳይቷል። ለአብነት በጅማ የተካሄደው ‘ፖሊዮን በጋራ እናጥፋ’ የሚለውን የጤና ጉዳይን ያነሳ ነበር። በአዳማ ከተማ የተከናወነው ሁነት ደግሞ በመኪና ውድድር ታጅቦ የተከናወነና የቱሪዝም መስህቦችን ማስተዋወቅን ታላሚ ያደረገ ነበር። ‘’ለሀዋሳ ከፍታ እንሮጣለን’’ በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ሁነትም ከጅማና አዳማው ሁነት የተለየ እሳቤንም ሆነ መልዕክትን አልያዘም። ሁሉም ሁነቶች ከዋነኞቹ አምስት ምጣኔ ሃብታዊ አምዶች መካከል አንዱ የሆነውን ቱሪዝም ልማት በማጠናከር የማህበረሰቡን የዘርፉ ተጠቃሚነት ማላቅን ታሳቢ ማድረጋቸውን መመልከት ተችሏል። ቅኝቶቻችን በወፍ በረር ይህንን ይመስላሉ!! የሳምንት ሰው ይበለን!!!
ትንታኔዎች
ለተቃና ነገ የኢትዮጵያ ትጋት አንዱ መገለጫ
May 11, 2026 1347
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ ከምትከውናቸው ዐበይት ጉዳዮች መካከል ሰው ተኮር ተግባራት ቀዳሚው ነው። በአዲስ አበባ በተካሄደው ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ጥረት ሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ ነው ብለዋል። መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል አድርጎ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በዚህም መሠረት፤ የልጆች ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት፣ የምገባ ሥርዓትን ማሳደግ፣ የሕጻናት መጫወቻ ሥፍራዎች ግንባታ ላይ ተጨባጭ ውጤቶች መምጣታቸውንም ነበር የጠቀሱት። ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማትና ትምህርት ፖሊሲ የዘላቂ ብልጽግና መንገዳችን ከሆነው የመደመር ዕሳቤ ጋር በተናበበ መልኩ እየተተገበረ በስኬት ቀጥሏልም ብለዋል። ኢትዮጵያ ለነገ የተዘጋጀ ትውልድ ለመገንባት በሕግና በፖሊሲ የተደገፉ የቀዳማይ ልጅነት ኢኒሼቲቮችን እየተገበረች እንደምትገኝም አስታውቀዋል። ለአብነትም፤ በ2015 ተሻሽሎ የፀደቀው ሀገር አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ልማት እና ትምህርት የፖሊሲ ማዕቀፍ እንዲሁም በ2017 የፀደቀውን አጠቃላይ የትምህርት አዋጅ መሠረት በማድረግ ከ35ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላው ሀገሪቱ እየተተገበረ መሆኑን አንስተዋል። በመንግሥት ተቋማት የሕጻናት ማቆያ ማዕከላት ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በመጠቆምም፤ ኢትዮጵያ የሕጻናትን ደኅንነት ማሻሻል የሚያስችል ጉልኅ ብሔራዊ መርሐ-ግብር መጀመሯን አንስተዋል። በሰቆጣ ቃል ኪዳን አማካኝነት የ15 ዓመት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ ከሁለት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ላይ የሚደርሰውን መቀንጨር በ2022ዓ.ም ዜሮ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት። የሌማት ትሩፋትና የአልሚ ምግቦች ምርታማነት የሕጻናትን ጉዳት ለመቀነስና የልጆችን ጤናማነት መጨመር እያስቻሉ እንደሚገኙም ነው የተናገሩት። ኢትዮጵያ ለዘላቂ የልማት ግቦችና ለሕጻናት መብቶች ጥበቃ የገባቻቸውን ቃል ኪዳኖች ወደ ተግባር እየለወጠች መሆኑን በማንሳት፤ ይህንንም አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። መንግሥት ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የቀዳማይ ልጅነት ልማትን በመላ ሀገሪቱ ለማስፋት ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑንም አመላክተዋል። በዚህም መሠረት፤ በጀት በመመደብ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል፣ የተማሪዎችን ምገባ በማስፋፋት ውጤት ማምጣቱን ነው የሚያብራሩት። ልጆች በአካልና በመንፈስ የሚጎለብቱባቸው የስፖርትና የመዝናኛ ቦታዎች በየአካባቢው በመገንባት፣ በኮሪደር ልማት ለልጆች ምቹ ሥፍራ እየተፈጠረ መሆኑንም በመጥቀስ። ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር፣ አኅጉር እና ዓለም ላይ መሥራት በመሆኑ በትጋት ማስቀጠል እንደሚገባም በአጽንኦት ይናገራሉ። አፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ተግዳሮቶችን ለመፍታት የራሷን መፍትሔዎች በማፍለቅ፣ በብሔራዊ የልማት አጀንዳዋ እያካተተች መሆኑን የሚገልጹት ደግሞ የአፍሪካ ቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ከበደ ወርቁ ናቸው። በሕጻናት ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ማንኛውም ሀገር በመጪው ትውልድ ላይ ሊያደርጋቸው ከሚችላቸው እጅግ አስፈላጊ ኢንቨስትመንቶች አንዱ መሆኑንም ያነሳሉ። አፍሪካ በቀዳማይ ልጅነት ልማት ላይ ያሉባትን ተግዳሮቶች ከመጋፈጥ ባለፈ፤ የራሷን መፍትሔዎች እያመነጨች መሆኑንና ጉዳዩን የብሔራዊ ልማት አጀንዳዋ አካል እያደረገችው እንደምትገኝም ገልጸዋል። አዲስ አበባ ይህን ዓለምአቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ እንድታስተናግድ የተመረጠችበት ዋና ምክንያትም፤ በዘርፉ እያከናወነች ያለው ተግባር አርዓያነት ያለው በመሆኑ ነው ብለዋል። ከተማዋ የጤና እና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎቶችን ያካተተ የተቀናጀ ዘርፈ-ብዙ አሠራር መዘርጋቷን ጠቅሰው፤ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት እና የቀን የሕጻናት እንክብካቤ ማዕከላትን በከተማ አቀፍ ስትራቴጂ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝም ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው፤ መዲናዋ በቀዳማይ ልጅነት ያመጣችው ተጨባጭ ውጤት በአርዓያነት እንድትጠቀስ እንዳደረጋት አንስተዋል። በሕጻናት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ዓመታት የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች፤ በትምህርት፣ በሰው ሃብት ልማትና በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ረጅም ጊዜ የሚቆይ ፋይዳ እንዳለውም አስረድተዋል። በዚህም በአዲስ አበባ ፍትሐዊና አካታች የቀዳማይ ልጅነት ልማት መርሐ-ግብርን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ የትውልድ ግንባታ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል። "ሕጻናት የአዲስ አበባ የነገ ተስፋዎች" የሚል ፍኖተ ካርታ በመቅረጽ 1 ነጥብ 3 ሚሊየን ለሚሆኑ ከስድስት ዓመት በታች ሕጻናት ሁለንተናዊ ዕድገት መረጋገጥ እየተሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በትምህርት ቤት ምገባ መርሐ-ግብርም ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ ዩኒፎርምና በቀን ሁለት ጊዜ ምግብ በማቅረብ በሕጻናት ክብካቤ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል ነው ያሉት። የሕጻናት ማቆያና መጫወቻ የመሠረተ-ልማት ግንባታ፤ ሕጻናት ነፃ የሕክምና፣ የምገባና የሥነ-ልቦና አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። የቀዳማይ ልጅነት መርሐ-ግብር በ2015 ዓ.ም ሲጀመር በዕድገት ወደ ኋላ የቀሩ የሕጻናት መጠን ከነበሩበት 13 በመቶ አሁን ላይ ወደ 10 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉን ከንቲባዋ አመላክተዋል። አክለውም፤ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዝግጁነታቸው ከነበረበት 49 በመቶ አሁን ወደ 90 በመቶ ማደጉንም ተናግረዋል። ሀገር በሁሉም ዘርፍ የበቃ መጪ ትውልድ እንዲኖራት መንግስት የያዘው ጥረት በሚፈለገው መጠን ለውጤት እንዲበቃ የሁሉንም ትኩረትና ተሳትፎ ይሻል። ለነገ በሁሉም ዘርፍ የዳበረ ትውልድና የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን ዛሬ ላይ እየተደረገ ያለው ርብርብ የሀገራችንን መፃኢ ብሩህ ተስፋ ይበልጥ የሚያለመልም ነውና ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።
ትኩረት የተሰጠው የሕጻናት ስነምግብ
May 10, 2026 465
በሙሴ መለሰ በዓለም ላይ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ህጻናት ሙሉ አካላዊ እና አዕምሯዊ አቅማቸውን ላይ ሳይደርሱ እድሜያቸውን ይቆጥራሉ። የዚህ ልብ ሰባሪ ክስተት መነሻ መቀንጨር (stunting) ይባላል። የስነ ምግብ ባለሙያዎች መቀንጨርን በዓለም አቀፍ ደረጃ ስር የሰደደ ቀውስ ያስከተለ እና የጉዳቱ መጠን የገዘፈ ነገር ግን የአስከፊነቱን ያህል በቂ ትኩረት ያላገኘ ጉዳይ ነው ይሉታል። ብዙ እንደ ግጭቶች እና ሌሎች የዓለም ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ቀውሶች አርዕስተ ዜና ሲሆን አይታይም። በቀላሉም የህዝብን ትኩረት አይስብም። ይሁንና የመቀንጨር ጉዳቶች ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ መዘዞች እና የአንድ ሀገር ልማትና ጉዞ ላይ ሊቀለበስ የማይችል ጣጣን ያስከትላል። የህጻናትን ሰውነት ቀስ በቀስ እየጎዳ አዕምሯቸው እና የመፍጠር አቅማቸውን እያደከመ በመሄድ፣ በድምጽ አልባነቱ ውስጥ ውስጡን ዘላቂ መዘዝ እያመጣ ይገኛል። መቀንጨር ህጻናትን በለጋ እድሜያቸው ጊዜ ብቻ ጎድቶ የሚያበቃ ቢሆን መልካም ነበር ዳፋው እስከ ህይወታቸው መጨረሻ የሚከተላቸው ነው። ህጻናት እጅግ በጣም ቁልፍ በሚባለው የእድሜ ክልል ማለትም ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት ባለው ጊዜ ተመጣጣኝ ምግብ ማግኘት ሲገባቸው በምግብ እጦት ምክንያት እድገታቸው አሉታዊ ተጽእኖ ይደርስባቸዋል። የመቀንጨር ጉዳት አካላዊ ብቻ ጉዳት አድርጎ ማየት የችግሩን ሙሉ ምስል እንደማያሳይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ይገልጻል። የመቀንጨር ችግር ያለባቸው ህጻናት ትምህርታቸውን በሚገባ መከታተል እንደማይችሉና በሽታ ተጋላጭነታቸው የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ከሚያገኙ ህጻናት ጋር ሲነጻጻር እጅጉን ሰፊ እንደሆነ አመልክቷል። የአዕምሮ እድገት ውስንነት በማምጣት አቅማቸውን በሚገባ አውጥተው እንዳይጠቀሙ ያደርጋል። ህጻናት በምግብ እጦት መቀንጨራቸውን ዩኒሴፍ የህጻናት መብቶች ጥሰት ሲል ይገልጸዋል። ይህም ትውልድ ለአንድ ሀገር የሚኖረው ድርሻ እንዲኮስስ ያደርጋል። መቀንጨር ድምጽ የለውም ኢኮኖሚን በአንድ ጊዜ አያቃውስም ወይንም ህዝብ ላይ ቶሎ ስጋትን አይጭርም ግን ጉዳቱ አያሌ ነው። በዓለም ላይ ከአምስት ዓመት በታች ከሚገኙ ህጻናት መካከል 23 ነጥብ 2 በመቶው የመቀንጨር ሰለባ መሆናቸውን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያመለክታል። ይህ ችግር የህጻናትን አካላዊና አዕምሯዊ አቅም ከመንጠቅ ባለፈ፣ የሀገርን የረጅም ጊዜ እድገት ወደ ኋላ የሚጎትት መዋቅራዊ ሳንካ ሆኖ ቀጥሏል። በኢትዮጵያ መቀንጨርን ማጥፋት ከምግብ እና ጤና ግቦች በዘለለ ሀገር እንድትበለጽግና እንድታድግ ከሚደረገው ብሄራዊ ውጥን ጋር የተቆራኘ የህልውና ጉዳይ ነው። የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ እድገት መሳካት የጀርባ አጥንት ለሆነው አምራች እና ተመራማሪ ሀይል ግንባታ ያለው አስተዋጽዖ ከፍ ያለ መሆኑ ይታመናል። ምንም እንኳ በሀገራችን የመቀንጨር ምጣኔ እ.አ.አ በ1990ዎቹ ከነበረበት 60 በመቶ ወደ 39 በመቶ ቢቀንስም፣ አሁንም ችግሩ ሙሉ በሙሉ ያልተወገደ መሆኑ ይታወቃል። ይህንን አስከፊ አዙሪት ለመስበር በ2007 ዓ.ም የሰቆጣ ቃል ኪዳን የተሰኘ ታሪካዊ መርሃ ግብር ይፋ ተደርጓል። ይህ ታሪካዊ ቃል ኪዳን በ15 ዓመታት ፍኖተ ካርታ ውስጥ ሦስት ዋና ዋና የትግበራ ምዕራፎችን አካትቶ የያዘ ነው። የመጀመሪያው የኢኖቬሽን ምዕራፍ (2010-2013 ዓ.ም) በ40 ወረዳዎች ላይ ትኩረት በማድረግ የባለድርሻ አካላትን ቅንጅታዊ አሰራር ውጤታማነት ያረጋገጠበት ሲሆን፣ ቀጥሎ የመጣው የማስፋፋት ምዕራፍ (2014-2018 ዓ.ም) የትግበራ ሽፋኑን ወደ 314 ወረዳዎች አሳድጓል። በዚህ ምዕራፍ በ2017 በጀት ዓመት ብቻ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ህጻናት እና 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን እናቶችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል። በአሁኑ ወቅት የተጀመረው የመጨረሻው የማስፋት ምዕራፍ (2019 – 2023 ዓ.ም) ደግሞ የተገኙ ልምዶችን በመቀመር እና ማህበረሰቡን በባለቤትነት በማሳተፍ መቀንጨርን በኢትዮጵያ ዜሮ ለማድረግ የታለመበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ነው። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን፣ ስርዓተ ምግብና ሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ የጤና መድህን፣ የጽዱ ኢትዮጵያ የማስፋፊያ አድቮኬሲና የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ማሻሻያ የ2018 ዓ.ም የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀምን በተመለከተ በበይነ መረብ ውይይት አካሂደው ነበር። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚ ወቅት የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ እድገት መሳካት የጀርባ አጥንት ለሆነው አምራች እና ተመራማሪ ኃይል ግንባታ ያለው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ መሆኑን አንስተዋል። በውይይቱ ላይ ከተነሱት ጉዳዮች አንዱ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ነበር። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ትግበራ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ገልጸው በዚህም በቃል ኪዳኑ የ15 ዓመት ፍኖተ ካርታ መሰረት የመጨረሻው የአምስት ዓመት የማስፋት ምዕራፍ (2019 – 2023 ዓ.ም) የትግበራ ማስፈፀሚያ እቅድ መጽደቁን ጠቅሰዋል። በዚህም የመቀንጨርንና ሌሎች የስርዓተ ምግብ ችግሮች ምጣኔን በፍጥነት ለመቀነስ የተገኙ ልምዶች በመቀመር፣ ማህበረሰቡን በባለቤትነት የማሳተፍ ስራን ማጠናከር እንደሚገባም አንስተዋል። የሰቆጣ ቃል ኪዳን ስኬታማነት ኢትዮጵያ በዓለም ስርዓተ ምግብ ውስጥ ታሪካዊ አሻራ እንድትጥል ከማድረጉም ባለፈ፣ ጤናማ፣ ምርታማና የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ የሚገነባ ብቁ ትውልድ ለማፍራት ዋስትና የሚሰጥ ነው። ይህ ጉዞ ከመንግስት የፖለቲካ ቁርጠኝነት ባለፈ፣ መላው ማህበረሰብ እና ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ድጋፋቸውን በማጠናከር ለመጪው ትውልድ የገቡትን የህልውና ቃል ኪዳን በተግባር የሚመሰክሩበት ነው። በአጠቃላይም በአሁኑ ሰዓት የህጻናት መቀንጨርን ለመከላከልም ሆነ አጠቃላይ ምግብን በዓይነትም ሆነ በጥራት በገበታ ሙሉ ለማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት በመላው ሃገሪቱ እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት በዚህ ረገድ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ድህነትን ማሸነፍ ሃገራዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ ግቧ የሆነው ሃገራችን በሁሉም መስክ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት የምግብ ሉዓላዊነቷን በማረጋገጥ የዜጎችን ጤንነት በተሟላ መልኩ ማስጠበቅ የሚያስችላትም ነው።
ባሳለፍነው ሣምንት ...
May 9, 2026 695
ከሚያዝያ 25 እስከ ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … · ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የዘንድሮው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ባሳለፍነው ሳምንት የተከፈተ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ፤ ውጤት ተኮር አመራራችን ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ የኢንዱስትሪ መስፋፋት ተንጸባርቋል ብለዋል። የአምራች ኢንዱስትሪዎች አማካይ የማምረት ዐቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ በማድረግ፣ ባለፉት አራት ዓመታት ከ2 ሺህ 800 በላይ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ ተችሏል ብለዋል። ኤክስፖው ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ ንቁ አምራቾችን እና ስታርትአፖችን በጨመረ ዐቅም በአንድነት ማሰባሰቡን ጠቁመው፤ በጋራ በመሆን ይህንን ጠንካራ መነቃቃት በማስቀጠል ለሚመጣው ትውልድ ጽኑ፣ በኢንዱስትሪ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን እንገነባለን ብለዋል። · 85ኛው የጀግኖች ዓርበኞች በዓል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለ85ኛው የጀግኖች ዓርበኞች በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት፤ ሚያዝያ 27 ቀን ኢትዮጵያውያን ጀግኖች ዓርበኞች የፋሽስትን ወረራ የቀለበሱበትና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ያስከበሩበት በዓል መሆኑን አውስተዋል። አሁን ላይ የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲሳካ ብሔራዊ ዓርበኞችን ይፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የራስ ፍላጎትን፣ ባንዳነትን እና ወራሪን እምቢ የሚል ዓርበኝነት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የኢንዱስትሪ ዓርበኞች፣ የግብርና ዓርበኞች፣ የጸጥታ ዓርበኞች፣ የፖለቲካ ዓርበኞች፣ የንግድ ዓርበኞች፣ የዲፕሎማሲ ዓርበኞች፣ የመንግሥት አገልጋይ ዓርበኞች፣ የሕክምና ዓርበኞች፣ የትምህርት ዓርበኞች፣ ወዘተ. . . ያስፈልጉናል ሲሉም አብራርተዋል። ይህን በዓል የምናከብረው የየራሳችንን የዓርበኝነት ደረጃ በመገምገም ነው፤ በዚህም መሠረት ለኢትዮጵያ ምን ያህል ዓርበኞች ነን? ማለት ይገባናል ብለዋል በመልዕክታቸው። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባስተላለፉት የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ዓርበኞቻችን ታሪክ የሠሩት የውስጥ ባንዳንና የውጭ ባዳን ድል ነሥተው ነው፤ እኛም የአባቶቻችን ልጆች በመሆናችን አሁንም ያንን ድል እንደግመዋለን ብለዋል። ዛሬ የዓርበኝነት ትርጉሙ ዘርፈ ብዙ ሆኗል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የዚህ ዘመን ዓርበኝነት በሥራ መትጋትና በዕውቀት መመራት፣ የድህነትን ታሪክ ለመቀየር ቆርጦ መነሣት፣ የተሻለች የነገዋ ኢትዮጵያን በላባችን መገንባት ነው ሲሉም አስረድተዋል። ስለሆነም በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና በዲፕሎማሲ መስኮች ድልን እያስቀጠልን፤ በተደመረ ዐቅም ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ ማማ የሚያወጣ የዘመኑ ዓርበኛ ልንሆን ይገባል ነው ያሉት። · የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጥረት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱልልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሔክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ማሳን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የጀመርነው ጥረት በላቀ ውጤት ቀጥሏል ብለዋል። · የኢትዮጵያና አዘርባጃን ግንኙነት በይበልጥ መጠናከር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ከኔዘርላንድስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮብ ጄተን ጋር ውጤታማ የሥልክ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ መመክራቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚያስችሉ መንገዶች ላይ ሐሳብ ተለዋውጠናል ብለዋል። ·የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት፤ የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ በሚል መሪ ሐሳብ ባለፉት ዓመታት በሚዲያ ዘርፍና ተቋማት ላይ የተመዘገቡ ስኬቶች የቀረቡበት የምክክር መድረክ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት የሚዲያ ምኅዳሩን በዴሞክራሲያዊ ዐውድ ለመዋጀት በወሰድነው እርምጃ ለሀገር ግንባታ የሚረዳ መሠረት ተጥሏል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ውጤት እንዲቀጥልም ሚዲያዎች ከዋልታ ረገጥነትና ከጽንፈኝነት ወጥተው በእውነት ላይ የተመሠረተ ትርክት በመገንባት፣ ለጋራ ማንነትና ለብሔራዊ መግባባት በቁርጠኝነት ሊሠሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። ሚዲያዎቻችን በሰው ሠራሽ አስተውሎት እና በጥናት የታገዘ ጥልቅ ትንተና በማቅረብ፣ ከአርዕስት ሽያጭ ባለፈ ለሀገር አጀንዳዎች ትኩረት መስጠት ይኖርባቸዋልም ነው ያሉት። ተግባራቸውም በዓላማ፣ በዕይታ፣ በሙያዊ ብቃትና ለሕዝብ ቅርብ በመሆን ላይ ተመስርቶ፣ ሚዛናዊነትን በጠበቀ መልኩ ለሀገር ብልጽግና መንገድ ጠራጊና ችግር ፈቺ ሆነው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጂቡቲው ፕሬዚዳንት በዓለ ሢመት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት በተመራጩ የጂቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ በዓለ ሢመት ሥነ-ሥርዓት ለመታደም ወደ ጅቡቲ አቅንተዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባስተላለፉት መልዕክትም፤ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ለሀገራቸው የሚሰጡት አገልግሎት ሁለንተናዊ እድገትን እንዲያስቀጥል ልባዊ ደስታዬንና መልካም ምኞቴን ልገልጽ እወዳለሁ ብለዋል። በኢትዮጵያ እና በጂቡቲ መካከል ያለው የቆየ ወዳጅነት እና ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለሕዝቦቻችን የጋራ ብልጽግና እንዲሁም ለቀጣናችን ሰላምና መረጋጋት መጠናከር መሰረት እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል በመልዕክታቸው። · የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መመረቅ ሪዞርቱ ባሳለፍነው ሳምንት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመረቀ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ለባሕር ዳርና ለአካባቢው ዘርፈ ብዙ ትሩፋት ይዞ የመጣ መሆኑን ተናግረዋል። የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መንግሥት ለቱሪዝም መዳረሻዎች የሰጠው ትኩረት ምን ውጤት እንዳመጣ በገሐድ የሚነበብበት ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸው፤ የአካባቢውን የቱሪዝም መሥመርና ሠንሠለት የሚያጠናክር ማረፊያና መዳረሻ ነው ብለዋል። ሪዞርቱ ዘመናዊ እና ቅንጡ የእንግዳ ማረፊያዎች፣ የመዝናኛ ሥፍራዎች፣ ሱቆች፣ አምፊ ቴአትር እና መሰል መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ ጣናን ተንተርሶ የተሠራ መሆኑንም አብራርተዋል። በተመሳሳይ ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚያው በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ደረጃውን ያሟላ Four Points by Sheraton ሆቴል የግንባታ ፕሮጀክት በይፋ አስጀምረዋል። በርካታ አገልግሎቶችን አሟልቶ በ18 ወራት ግንባታው የሚጠናቀቀው ይህ ሆቴልም የግል ባለ ሀብቱ በሀገራችን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ውስጥ ያለውን ሚና የሚያሳይ ነው ብለዋል። ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በተለያዩ ዘርፎች እያመጣ ያለውን ለውጥ አድንቀው፤ ይህ የሆቴል ግንባታም ለባሕር ዳር በጸጋ ላይ ጸጋ የሚጨምር መሆኑን ተናግረዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ዓለም አቀፍ ኤክስፖ ማጠቃለያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሰላፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአራተኛው የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ዓለም አቀፍ ኤክስፖ ማጠቃለያ ላይ የተመለከትናቸው የጥራትና የፈጠራ ውጤቶች የሀገራችንን የማምረት ዐቅም የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ ታምርት የሉዓላዊነታችን መሠረት የብልጽግናችን ምሦሶ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪ ዘርፍ እያሳየችው ያለው ተጨባጭ ዕድገት የብልጽግናችን ማብሠሪያ እየሆነ ይገኛል ሲሉ ገልጸዋል። የሀገር ሉዓላዊነትና ነጻነት በምልዓት የሚረጋገጠው በምርት ራስን በመቻል መሆኑን በመገንዘብ የተጀመረው ይህ ንቅናቄ፤ ተኪ ምርትን በማሳደግ፣ የፋብሪካዎችን ዐቅም በመገንባት እና የሥራ ባህልን በመለወጥ ረገድ ከፍተኛ ስኬት ማስመዝገቡን አስታውቀዋል። መንግሥት ለዘርፉ ምቹ ፖሊሲዎችንና ድጋፎችን ማመቻቸቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠው፤ ቀጣዩን ኤክስፖ ይበልጥ በፈጠራና በስብጥር የላቀ ለማድረግ እንሠራለን ሲሉ አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ
የ471 ሚሊዮን ተከታዮች ባለቤት የሆኑ የ30 ሀገራት ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሳተፉበት ታሪካዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ
May 6, 2026 653
በመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS 2026) ላይ ለመሳተፍ፣ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡና በአጠቃላይ 321 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 61 ታዋቂ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ወደ አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። እነዚህንም 150 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 120 ታዋቂ ኢትዮጵያውያን የማህበራዊ ሚዲያ የይዘት ፈጣሪዎች ይቀላቀሏቸዋል። ታሪካዊው ጉባኤ ነገ እና ከነገ በስቲያ በአድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ጉባኤው በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ እና በኤጂኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ የጋራ ትብብር የተዘጋጀም ነው። በአፍሪካ የዲፕሎማሲ ማዕከል አዲስ አበባ የሚካሄደው ይህ ጉባኤ የአፍሪካን ዲጂታል የወደፊት ዕጣ ፈንታ እንደገና ለመቅረጽ ያለመ ነው። ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበር እና የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅበት ስም ነው) ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገብቷል። ሴራሊዮናዊው ቦይዜ ክሪሽ፣ ቤኒናዊቷ ሬጌ ቦይዘር፣ ሴኔጋላዊው ጃው ኬቹፕ እና ስዊዛላንዳዊው ጎጎ እስዋቲኒ ኤምኤም ሌሎች ለጉባኤው የገቡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖፐ ፈጣሪዎች ናቸው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎቹ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል። ጉባኤው በአፍሪካ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሰባሰቡበት፣ ስለራሳቸውና ስለ አፍሪካ የሚናገሩበት፣ እንዲሁም ስለ ይዘት ፈጠራና ስለሚገጥሟቸው ተግዳሮቶች የሚወያዩበት መድረክ ነው። ይህም ተጽእኖ ፈጣሪዎቹን በአንድ መድረክ የማገናኘት ትልቅ አጋጣሚን ፈጥሯል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በመጠቀም የይዘት ፈጣሪነት የወደፊት ሁኔታ፣ የአፍሪካ አዎንታዊ ገጽታን መገንባት እና የዲጂታል ተጽዕኖን ከአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ ጋር ማጣጣም በሚሉ ጉዳዮች ላይ ሶስት የከፍተኛ ደረጃ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ። ጉባኤው "በችግር ላይ የተመሰረተ" ዘገባን በእውነተኛ የአፍሪካ የዕድገት ታሪኮች ለመተካት የታለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑም ተመልክቷል። የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ የኢትዮጵያን ቱሪዝም በከፍተኛ ሁኔታ የማስተዋወቅ እድሉ ሰፊ ነው። እነዚህ የይዘት ውጤቶች የአፍሪካን መልካም ገጽታ ለዓለም፣ የኢትዮጵያንም መልካም ገጽታ ለአፍሪካውያን ማሳየት የሚችሉ ናቸው። ጉባኤው ሐሙስ ዕለት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚጀመር ሲሆን፣ ከ470 ሚሊዮን በላይ የዲጂታል ተከታዮች አይኖች በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ላይ አርፈዋል። ይህም አፍሪካ የራሷን ታሪክ ራሷ መተረክ የጀመረችበት አዲስ ዘመን ማሳያ ሆኗል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 5218
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 3364
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 9154
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 7637
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 1510
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 1276
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።