ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የውጭ ሃገራት ፍልሰት በህጋዊ ሥርዓት እንዲመራ የተሰራው ሥራ ውጤት እያመጣ ነው 
Jan 13, 2026 70
ሆሳዕና፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦የዜጎችን ሰብአዊ መብትና ክብርን ለማስጠበቅ የውጭ ሃገራት ፍልሰት በህጋዊ ሥርዓት እንዲመራ የተሰራው ሥራ ውጤት እያመጣ መሆኑን የፍትህ ሚኒስቴር ገለፀ። በሰው የመነገድ ወንጀልን በመከላከልና በዳያስፖራ ተሳትፎ ላይ የሚመክር የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው። በዚህ ወቅት የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ እንዳሉት፤ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ተለያዩ ሃገራት በፍልሰት የሚሄዱ ዜጎች ሰብአዊ መብታቸውና ክብራቸው ተነክቶ ለእንግልት እና ለሞት እየተዳረጉ ነው።   ችግሩን ለመከላከልና ለመቀነስ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፍ አዋጆችን ከመተግበር ባለፈ በሀገሪቱ በአዲስ መልክ ብሔራዊ ምክር ቤት እና የትብብር ጥምረት ጽህፈት ቤት ተቋቁሞ በቅንጅት በተሰራው ሥራ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል። ከዚህ ጎን ለጎን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሥራ ዕድሎችን በማስፋት የዜጎች ፍልሰት ጫናን ለመቀነስ መቻሉን አውስተዋል። ከስደት ተመላሽ ዜጎችን የማቋቋም ሥራ ትኩረት እንደተሰጠው በመጠቆም ወንጀል ፈጽመው በተለያዩ ሃገራት የሚገኙ ዜጎች ከሚገኙበት ሀገራት ጋር በመቀናጀት ተጠያቂ የማድረግ ሥራም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍፁም አረጋ፤ በርካታ ዜጎች በህገ ወጥ ደላሎች ተታለው ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ከዚያም ባለፈ ለህልፈት እየተዳረጉ መሆናቸውን ገልጸው፣ እነዚህን ዜጎች ለመታደግ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።   ለስደት ገፊ ምክንያቶችን በመለየት በሃገር ውስጥ እና በተለያዩ ሃገራት በህጋዊ መንገድ የሥራ ባለቤት እንዲሆኑ እየተሰራ ያለውን ሥራም በማሳያነት ጠቅሰዋል። ከተለያዩ ሀገራት ጋር የጋራ ቅንጅት በመፍጠር የህገ ወጥ ስደት አሳሳቢነት ከማስገንዘብ ባለፈ በችግር ውስጥ ያሉ ዜጎችን ወደ ሃገር ውስጥ የመመለስ ሥራም ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የዳያስፖራው ተሳትፎ እያደገ መሆኑንም ገልጸዋል።   በህጋዊ መንገድ የሚላክን ገንዘብ ለማሳደግ በተሰራው ሥራም በተያዘው በጀት ዓመት ግማሽ ዓመት ህጋዊ የገንዘብ ዝውውሩ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተናግረዋል። በርካታ ዳያስፖራዎች በሀገር ውስጥ በኢንቨስትመንት ዘርፍ እንዲሳተፉ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም መዋዕለንዋያቸውን በማፍሰስ ለዜጎችም የሥራ ዕድል እየፈጠሩ መሆኑን አስረድተዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ በበኩላቸው፤ በክልሉ በሰው የመነገድ ወንጀል የሚሳተፉ ዜጎችን ተጠያቂ የማድረግ ሥራ እየተሰራ ነው።   በተለያየ ምክንያት ተታለው በህገ ወጥ መንገድ ወደውጭ ሀገር የሚሄዱትን ከመከላከል ባለፈ ዜጎች ለሥራ ወደውጭ ሲሄዱ ህጋዊ አሰራርን እንዲከተሉ የማስገንዘብ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል ። እንደእሳቸው ገለጻ፤ ከህገወጥ ፍልሰት ጋር በተያያዘ የሚታየውን ችግር ለመቀነስ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ሥራ እየተሰራ ነው። ለሁለት ቀናት እየተካሄደ ባለው የምክክር መድረክ የፌደራልና የክልሉ የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች፣ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የስደት ተመላሾችና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በመሳተፍ ላይ ናቸው። በተጨማሪም በደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ፣ ዚምባብዌና ታንዛንያ የሚገኙ የኢትዮጵያ አምባሳደሮች በቨርችዋል እየተሳተፉ ነው።
መንግስት የመንግስት ሠራተኞችን የቤት ችግር ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ
Jan 13, 2026 34
ግራዋ ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦የክልሉ መንግስት የመንግስት ሠራተኞችን የቤት ችግር ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ሲሉ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አሰፋ ገለጹ፡፡ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የግራዋ ከተማ አስተዳደር በማህበር ለተደራጁ 336 የመንግስት ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ሰጥቷል። የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አሰፋ በቦታ ርክክብ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ የክልሉ መንግስት የመንግስት ሠራተኞችን የቤት ችግር ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።   ለመንግስት ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ መሰጠቱ ሠራተኛው የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ በማድረግ በስራው ላይ ፍትሐዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችለዋል ብለዋል። የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ሚስኪ መሐመድ በበኩላቸው፤ ለሠራተኞቹ የተሰጣቸው መሬት ከመኖሪያ ቤት ጋር በተያያዘ ሲነሱ የነበሩ የዜጎች ጥያቄን የሚያቃልል መሆኑን አመልክተዋል። የሠራተኞች የቤት ጥያቄ መፈታት በተሰማሩበት መስክ ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ለማሻሻል ያግዛል ነው ያሉት።   በዛሬው እለት የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ የተሰጣቸው መምህራን፣ የጤና ባለሙያዎች፣ የፀጥታና የፍትህ አካላት ሲሆኑ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ በማግኘታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል። በዚህም ከመንግስት ጋር በጋራ በመሆን ልማትን እንደሚያፋጥኑ ገልጸው፣ በተሰማሩበት ሥራ ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ ዘርፉን በኢኖቬሽን የመደገፍ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jan 13, 2026 45
ቢሾፍቱ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ ዘርፉን በኢኖቬሽን የመደገፍ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ ገለፁ። ሀገር አቀፍ የጤና አገልግሎት ጥራት እና ኢኖቬሽን ጉባኤ በኦሮሚያ ጤና ቢሮ አዘጋጅነት በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ በመድረኩ እንደተናገሩት፤ የጤና አገልግሎት ጥራትን በማሻሻል ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከል ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። የጤና አገልግሎት ጥራቱን ለማሻሻል ኢኖቬሽንና ዲጂታላይዜሽን ላይ በስፋት በመስራት ፍትሃዊ ተደራሽነቱን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል። የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ኃላፊ ፕሮፌሰር ነጻነት ወርቅነህ በበኩላቸው፤ በክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ለዲጂታላይዜሽን፣ ለሰው ሃይል አቅም ግንባታና የሕክምና ግብአት ማሟላት ላይ በሰፊው መሰራቱን አንስተዋል።   የጤና አገልግሎት ጥራት ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍና አዳዲስ ፈጠራዎችን ወደ ስራ በማስገባት የተገልጋዩን እርካታ እውን ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። በጤና አገልግሎት ጥራት ፍትሃዊነትና ተደራሽነት ላይ የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል የጤና ኢኖቬሽን ስራዎችን ባህል ማድረግና ትብብሩን ማጠናከር እንደሚገባም ተናግረዋል። የጤናው ዘርፍ የኢኖቬሽን ስራዎችን የሚያሳዩ ኤግዚቢሽኖች፣ ጥናትና ምርምሮች እንዲሁም ትብብርን የሚያጠናክሩ ውይይቶችና ሌሎች ሁነቶች በጉባኤው ይካሄዳሉ ብለዋል። በጉባኤው ላይ የፌዴራልና የክልል አመራሮች፣ የዓለም ጤና ድርጅትና ዩኒሴፍ ተወካዮች፣ የምርምር ተቋማት፣ የግሉ ሴክተር እና ግብረሰናይ ድርጅቶች ተሳትፈዋል።
በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል
Jan 13, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ ምክክር መድረክ በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ እና በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እየተካሄደ ነው።   በመርሀ ግብሩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ ምክትል አፈ ጉባዔ ሎሚ በዶ፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር)፣ የክልሎች አፈ ጉባኤዎችና ምክትል አፈ ጉባኤዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ "የሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ዝግጅትና የምክር ቤቶች ሚና" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል። ምክትል ሰብሳቢው በገለፃቸው፤ ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የመራጮች ምዝገባ እንዲከናወን እና የድምፅ መስጫው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሆን ቦርዱ መወሰኑን አስታውቀዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይሄንን ታሳቢ በማድረግ የግብዓት ማሟላት፣ የስልጠናና ግንዛቤ የመፍጠሪያ የተለያዩ ዝግጅቶችን ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም ቦርዱ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ከመደበኛ የምርጫ ጣቢያዎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ በሥራ ምክንያት በተለያየ ቦታ የሚገኙ ዜጎች፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና ሌሎች ልዩ የምርጫ ጣቢያ ሊቋቋምላቸው የሚገባ ስለሆነ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር መስራታቸውን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ50 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚኖሩ የገለጹት ምክትል ሰብሳቢው፤ በአዋጁ መሰረት እያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ ከ 1 ሺህ 500 የማይበልጥ መራጭ መያዝ አለበት ብለዋል። በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት የምርጫ ስራዎችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ለቦርዱ አቅም የሚፈጥሩ ድንጋጌዎች መካተታቸውን ገልጸዋል። በዚህም የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባ እንዲሁም ሌሎች የቦርዱን ስራ ውጤታማ ሊያደርጉ የሚችሉና የቅሬታ አፈታት ስልቶች ማሻሻያ እንደተደረገባቸው ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ቦርዱ በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ምርጫውን ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት ማድረጉን ተናግረዋል። መራጮች በዲጂታል ወይም በአካል በመቅረብ መመዝገብ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መተግበሪያ አማካኝነት ባሉበት ሆነው መመዝገብ የሚፈልጉ መራጮች የብሔራዊ መታወቂያ ሊኖራቸው እንደሚገባ ገልጸዋል። በቦርዱ የተመለመሉ የምርጫ አስፈፃሚዎች ከማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ገለልተኛ የሆኑ ለስራው በቂ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውና የአካባቢውን የስራ ቋንቋና ባህል የሚያውቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።በመላ ሀገሪቱ ቢያንስ 318 ሺህ ምርጫ አስፈፃሚ እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡ የፖለቲካ ፖርቲዎች የፅሁፍና የቃል ፈተናውን ያለፉ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ገለልተኝነት በተመለከተ አስተያየት እንዲሰጡ ተደርጓል ብለዋል።
በከተማና ገጠር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሠረተ ልማቶች ለውጤት እየበቁ ነው
Jan 13, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦በከተማና ገጠር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሠረተ ልማቶች ለውጤት እየበቁ መሆናቸውን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ። በሀገር አቀፍ ደረጃ በ 76 ከተሞች ውጤታማ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የተገነባውን የመኖሪያ መንደርና ሌሎች የከተማና ገጠር የልማቶችን በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ በከተማና ገጠር ሰው ተኮር የልማት ሥራ ከተሞችን በማስዋብ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ሰፋፊ የልማት ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል። ለአብነትም በአማራ ክልል ሰቆጣ ከተማ፣ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ እንዲሁም ሐረር ከተማን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ መኖሪያ ቤቶች መገንባታቸውን አስታውቀዋል። በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብርም በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የቱሉ አራራ የተቀናጀ ሞዴል መንደር ተገንብቶ ለህዝብ ክፍት መደረጉን ተናግረዋል። የአዲስ አበባን ውጤታማ የኮሪደር ልማት በምሳሌነት በመውሰድ በ76 ከተሞች የሚገነባው የኮሪደር ልማት ሥራም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን አንስተዋል። የከተሞች የኮሪደር ልማትም በሥራ ዕድል ፈጠራና በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከሚፈጥሩት አቅም ባሻገር በከተሞች መካከል ጤናማ ውድድር እንዲኖር እያደረገ መሆኑን አብራርተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በከተማና ገጠር የሚገነቡ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የኢትዮጵያን የተሟላ ብልጽግና ማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውንም አስረድተዋል።
የሚታይ
በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል
Jan 13, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ ምክክር መድረክ በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ እና በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እየተካሄደ ነው።   በመርሀ ግብሩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ ምክትል አፈ ጉባዔ ሎሚ በዶ፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር)፣ የክልሎች አፈ ጉባኤዎችና ምክትል አፈ ጉባኤዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ "የሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ዝግጅትና የምክር ቤቶች ሚና" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል። ምክትል ሰብሳቢው በገለፃቸው፤ ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የመራጮች ምዝገባ እንዲከናወን እና የድምፅ መስጫው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሆን ቦርዱ መወሰኑን አስታውቀዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይሄንን ታሳቢ በማድረግ የግብዓት ማሟላት፣ የስልጠናና ግንዛቤ የመፍጠሪያ የተለያዩ ዝግጅቶችን ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም ቦርዱ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ከመደበኛ የምርጫ ጣቢያዎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ በሥራ ምክንያት በተለያየ ቦታ የሚገኙ ዜጎች፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና ሌሎች ልዩ የምርጫ ጣቢያ ሊቋቋምላቸው የሚገባ ስለሆነ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር መስራታቸውን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ50 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚኖሩ የገለጹት ምክትል ሰብሳቢው፤ በአዋጁ መሰረት እያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ ከ 1 ሺህ 500 የማይበልጥ መራጭ መያዝ አለበት ብለዋል። በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት የምርጫ ስራዎችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ለቦርዱ አቅም የሚፈጥሩ ድንጋጌዎች መካተታቸውን ገልጸዋል። በዚህም የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባ እንዲሁም ሌሎች የቦርዱን ስራ ውጤታማ ሊያደርጉ የሚችሉና የቅሬታ አፈታት ስልቶች ማሻሻያ እንደተደረገባቸው ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ቦርዱ በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ምርጫውን ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት ማድረጉን ተናግረዋል። መራጮች በዲጂታል ወይም በአካል በመቅረብ መመዝገብ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መተግበሪያ አማካኝነት ባሉበት ሆነው መመዝገብ የሚፈልጉ መራጮች የብሔራዊ መታወቂያ ሊኖራቸው እንደሚገባ ገልጸዋል። በቦርዱ የተመለመሉ የምርጫ አስፈፃሚዎች ከማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ገለልተኛ የሆኑ ለስራው በቂ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውና የአካባቢውን የስራ ቋንቋና ባህል የሚያውቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።በመላ ሀገሪቱ ቢያንስ 318 ሺህ ምርጫ አስፈፃሚ እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡ የፖለቲካ ፖርቲዎች የፅሁፍና የቃል ፈተናውን ያለፉ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ገለልተኝነት በተመለከተ አስተያየት እንዲሰጡ ተደርጓል ብለዋል።
በከተማና ገጠር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሠረተ ልማቶች ለውጤት እየበቁ ነው
Jan 13, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦በከተማና ገጠር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሠረተ ልማቶች ለውጤት እየበቁ መሆናቸውን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ። በሀገር አቀፍ ደረጃ በ 76 ከተሞች ውጤታማ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የተገነባውን የመኖሪያ መንደርና ሌሎች የከተማና ገጠር የልማቶችን በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ በከተማና ገጠር ሰው ተኮር የልማት ሥራ ከተሞችን በማስዋብ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ሰፋፊ የልማት ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል። ለአብነትም በአማራ ክልል ሰቆጣ ከተማ፣ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ እንዲሁም ሐረር ከተማን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ መኖሪያ ቤቶች መገንባታቸውን አስታውቀዋል። በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብርም በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የቱሉ አራራ የተቀናጀ ሞዴል መንደር ተገንብቶ ለህዝብ ክፍት መደረጉን ተናግረዋል። የአዲስ አበባን ውጤታማ የኮሪደር ልማት በምሳሌነት በመውሰድ በ76 ከተሞች የሚገነባው የኮሪደር ልማት ሥራም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን አንስተዋል። የከተሞች የኮሪደር ልማትም በሥራ ዕድል ፈጠራና በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከሚፈጥሩት አቅም ባሻገር በከተሞች መካከል ጤናማ ውድድር እንዲኖር እያደረገ መሆኑን አብራርተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በከተማና ገጠር የሚገነቡ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የኢትዮጵያን የተሟላ ብልጽግና ማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውንም አስረድተዋል።
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች ተሳትፎ እንዲጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት እየተዘጋጁ ነው
Jan 13, 2026 74
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በግንቦት ወር ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች ተሳትፎ እንዲጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት እየተዘጋጁ መሆኑን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጠቅላላ ምርጫው ሂደት ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ ከወዲሁ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ለምርጫው ሂደት የቦርዱ የተሟላ ዝግጅት እንዳለ ሆኖ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትና አጠቃላይ የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎ ወሳኝ ነው። በዚህም መሰረት የዜጎች የምርጫ ተሳትፎ እንዲጠናከር በማድረግ በኩል በተለይም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዝግጁነት ምን ይመስላል ሲል ኢዜአ የሚለከታቸው አካላትን አነጋግሯል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ፤ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሂደት ሁነኛ መሰረት በሆነው የምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ሂደትም ዜጎች በቂ ግንዛቤ አግኝተው በእውቀት ላይ ተመስርተው መብታቸውን መጠቀም እንዲችሉ ድርጅቶቹ የማስተማርና የማስገንዘብ ስራ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። በዚሁ መሰረትም በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች ተሳትፎ እንዲጠናከር የሲቪክ ማህበራት የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት እየተዘጋጁ መሆኑን አንስተዋል። በባለስልጣኑ የታቀፉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ አጠቃላይ ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን እንደሚሰሩም ገልጸዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ54 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምርጫን የመታዘብ፣ እንዲሁም ህብረተሰቡን ለማስተማር ፈቃድ በመስጠቱ ምህዳሩን አስፍቶልናል ያሉት ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ታደሉ እጀታ ናቸው።   ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት ምክር ቤቱ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀቱን በመግለጽ። ለምርጫ ሂደት መሳካት የዜጎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት በቂ ግንዛቤ ኖሯቸው እንዲሳተፉ ድርጅቱ ሚናውን ይወጣል ሲሉም አክለዋል። የሲዳማ ክልል ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ማስረሻ ክብረት፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ ሂደት አወንታዊ አበርክቶ እንዲኖራቸው ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል።   በዚህም መሰረት የሲቪክ ማህበራት ሚናቸውን መወጣት የሚያስችል ዝግጁነት እንዳላቸውም ነው ጨምረው የተናገሩት። በአንድ ሀገር የምርጫ ሂደት ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሲቪክ ማህበራት ሚና የላቀ መሆኑ ይታመናል።
ባህላዊ እሴቶች የወል እውነቶችና የብሔራዊ ትርክቶች መሠረት ናቸው
Jan 13, 2026 50
ሚዛን አማን፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ ባህላዊ እሴቶች የወል እውነቶችና የብሔራዊ ትርክቶች መሠረት በመሆናቸው ለሀገር ግንባታ ያላቸውን ሚና ለማጉላት እየተሰራ ነው ሲሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። የቤንች ዘመን መለወጫ በዓል "ቢስት ባር" በሚዛን አማን ከተማ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ተከብሯል። በበዓሉ የተገኙት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር እንዳሉት ኢትዮጵያ የብዝኃ ባህሎች ማዕከልና የመቻቻል ማሳያ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት።   ለከፋፋይና ነጣጣይ ትርክት የማይመቹ ሕዝቦች መገኛ በመሆኗ በሁሉም አካባቢዎች በባህላዊ በዓላትና ሌሎች ኩነቶች አብሮነታችን ደምቆ መታየቱን እንደቀጠለ ነው ሲሉም አክለዋል። የብሔረሰቦች ባህላዊ እሴቶች ደግሞ የወል እውነቶችና የብሔራዊ ትርክቶች መሠረት በመሆናቸው ለሀገር ግንባታ ያላቸው ሚና ጎልቶ እንዲወጣ እየተሠራ ነው ብለዋል። ያሉንን የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች ወደ ጥቅም በመቀየር ለኢትዮጵያ ብልጽግና መስፈንጠሪያ እንዲሆኑ ማስቻል ይገባል ሲሉም ገልጸዋል። ዛሬ የተከበረው የቤንች ዘመን መለወጫ "ቢስት ባር" በዓል የደረሰን እህል ተከፋፍሎ በመቃመስ ወደ አዲስ ዓመት የሚሸጋገሩበት እንዲሁም ክረምቱን በሰላም ስለተሸጋገረ ምስጋና የሚቀርብበት እንደሆነ ተናግረዋል። የእርስ በርስ ግንኙነት የሚጠናከርበትና የይቅርታ በዓል በመሆኑ የጥላቻን ግድግዳ በማፍረስ ሰላም የማጽናት ዕሴቱ ከክልሉ አልፎ ለሀገር የሚጠቅም ነው ብለዋል።   የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በክልሉ ለብሔረሰቦች ባህል ልማት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ያለ ልዩነት የሚከበረው የቢስት ባር ለክልሉ ህዝቦች አብሮነት መጠናከር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ይዘቱን ሳይቀይር ለትውልድ እንዲተላለፍ እንደሚሰራም አመልክተዋል። በዓሉን በአብሮነት ስናከብር ድኅነትን ለማሸነፍ አቅም የምንፈጥርበት ጭምር መሆን አለበት ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ለቱሪዝም ልማት የሚሰጠውን ትኩረት በማጠናከር የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱንም አመልክተዋል። የቢስት ባር በዓል ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትርጉም ስላለው ያሉትን እሴቶች በማጎልበት ለትውልድ ለማስትላለፍ ይሠራል ያሉት ደግሞ የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሀብታሙ ካፍትን ናቸው።   ሌሎች ቱባ ባህሎችን ወደ አደባባይ በማውጣት የጥንታዊ አባቶቻችንን ጥበብና ፍልስፍና ለልማታችን ተደማሪ አቅም እንዲሆን በትኩረት ይሠራል ብለዋል። ከበዓሉ ታዳሚዎች መካከል ቡዛብ ደመላሽ እና ወጣት ሜሮን ሰይድ በዓሉ የማናውቃቸውን ጠቃሚ የቢስት ባር እሴቶችን እንድንረዳ አስችሎናል ነው ያሉት። ከሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ጋር በአንድነት የሚከበር በዓል በመሆኑ ትውፊታዊ ይዘቱን ሳይለቅ እንዲቀጥል የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል።
በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ8 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ እንዲገቡ ውሳኔ ተሰጥቷል
Jan 13, 2026 60
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በግማሽ ዓመቱ ከ262 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ከ8 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ እንዲገቡ ውሳኔ ማግኘታቸውን የክልሉ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ገለጸ። በዘርፉ ለመሰማራት ጥያቄ ላቀረቡ አካላት የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ የሰጠውን ውሳኔን አስመልክቶ የክልሉ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አህመድ ኢድሪስ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በክልሉ ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን ጨምሮ ከተሞችም ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እንቅስቃሴያቸውን እንዲያጠናክሩ የተደረገ ሲሆን፤ በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አማካኝነትም የኢንቨስትመንት አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ጥያቄ ላቀረቡ አካላት የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ በሁለት ዙር ውሳኔ መስጠቱን ገልጸዋል። የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ በጥቅምት ወር ባካሄደው የመጀመሪያ ዙር ስብሰባ ከ90 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 3ሺህ 163 ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ውሳኔ እንዲያገኙ አድርጓል። ፕሮጀክቶቹ በአሁኑ ወቅት አብዛኞቹ ህጋዊ ሂደቶችን አጠናቀው ስራ የጀመሩ ሲሆን በሙሉ አቅም ወደ ስራ ሲገቡ ከ200 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ ቦርዱ በታህሳስ ወር መጨረሻ ላይ ባካሄደው ስብሰባ 172 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 5ሺህ 158 ፕሮጀክቶች ፍቃድ እንዲሰጥ መወሰኑን ገልጸዋል። እነዚህ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በ45 ቀናት ውስጥ ህጋዊ ሂደቶችን አጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ እንደሚደረግ ገልጸው ፕሮጀክቶቹ በሙሉ አቅማቸው ስራ ሲጀምሩ ከ400ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ያስገኛሉ ብለዋል። በአጠቃላይ በግማሽ ዓመቱ ከ262 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ከ8ሺህ በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ፈቃድ ማግኘታቸውን አስረድተዋል። ወደ ኢንቨስትመንት እንዲገቡ የተወሰነው የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት፣ የሀገር ውስጥ ባለህብቶች፣ የተሻለ ሀብት ያፈሩ አርሶ አደሮች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ተሰማርተው ሀብት ያፈሩ ወጣቶች እንዲሁም የህብረት ስራ ማህበራት መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህ ፕሮጀክቶች ፈጥነው በሙሉ አቅም ወደ ስራ መግባት እንዲችሉ የመሬት እና ፋይናንስ አቅርቦት፣ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እና የሰለጠነ የሰው ሃይል የማቅረብ ስራ በቢሮው አማካኝነት እንደሚከናወንም አስረድተዋል። የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶቹ በአማዛኙ ተኪ ምርቶች ላይ አተኩረው እንዲሰሩ እንደሚደረግ አመልክተው፤ ፍቃድ ከተሰጣቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀቶች መካከል 148 የሚሆኑት በቡና ዘርፍ የሚሰማሩ መሆናቸውንም አክለዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል
Jan 13, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ ምክክር መድረክ በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ እና በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እየተካሄደ ነው።   በመርሀ ግብሩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ ምክትል አፈ ጉባዔ ሎሚ በዶ፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር)፣ የክልሎች አፈ ጉባኤዎችና ምክትል አፈ ጉባኤዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ "የሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ዝግጅትና የምክር ቤቶች ሚና" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል። ምክትል ሰብሳቢው በገለፃቸው፤ ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የመራጮች ምዝገባ እንዲከናወን እና የድምፅ መስጫው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሆን ቦርዱ መወሰኑን አስታውቀዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይሄንን ታሳቢ በማድረግ የግብዓት ማሟላት፣ የስልጠናና ግንዛቤ የመፍጠሪያ የተለያዩ ዝግጅቶችን ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም ቦርዱ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ከመደበኛ የምርጫ ጣቢያዎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ በሥራ ምክንያት በተለያየ ቦታ የሚገኙ ዜጎች፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና ሌሎች ልዩ የምርጫ ጣቢያ ሊቋቋምላቸው የሚገባ ስለሆነ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር መስራታቸውን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ50 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚኖሩ የገለጹት ምክትል ሰብሳቢው፤ በአዋጁ መሰረት እያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ ከ 1 ሺህ 500 የማይበልጥ መራጭ መያዝ አለበት ብለዋል። በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት የምርጫ ስራዎችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ለቦርዱ አቅም የሚፈጥሩ ድንጋጌዎች መካተታቸውን ገልጸዋል። በዚህም የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባ እንዲሁም ሌሎች የቦርዱን ስራ ውጤታማ ሊያደርጉ የሚችሉና የቅሬታ አፈታት ስልቶች ማሻሻያ እንደተደረገባቸው ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ቦርዱ በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ምርጫውን ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት ማድረጉን ተናግረዋል። መራጮች በዲጂታል ወይም በአካል በመቅረብ መመዝገብ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መተግበሪያ አማካኝነት ባሉበት ሆነው መመዝገብ የሚፈልጉ መራጮች የብሔራዊ መታወቂያ ሊኖራቸው እንደሚገባ ገልጸዋል። በቦርዱ የተመለመሉ የምርጫ አስፈፃሚዎች ከማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ገለልተኛ የሆኑ ለስራው በቂ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውና የአካባቢውን የስራ ቋንቋና ባህል የሚያውቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።በመላ ሀገሪቱ ቢያንስ 318 ሺህ ምርጫ አስፈፃሚ እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡ የፖለቲካ ፖርቲዎች የፅሁፍና የቃል ፈተናውን ያለፉ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ገለልተኝነት በተመለከተ አስተያየት እንዲሰጡ ተደርጓል ብለዋል።
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች ተሳትፎ እንዲጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት እየተዘጋጁ ነው
Jan 13, 2026 74
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በግንቦት ወር ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች ተሳትፎ እንዲጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት እየተዘጋጁ መሆኑን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጠቅላላ ምርጫው ሂደት ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ ከወዲሁ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ለምርጫው ሂደት የቦርዱ የተሟላ ዝግጅት እንዳለ ሆኖ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትና አጠቃላይ የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎ ወሳኝ ነው። በዚህም መሰረት የዜጎች የምርጫ ተሳትፎ እንዲጠናከር በማድረግ በኩል በተለይም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዝግጁነት ምን ይመስላል ሲል ኢዜአ የሚለከታቸው አካላትን አነጋግሯል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ፤ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሂደት ሁነኛ መሰረት በሆነው የምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ሂደትም ዜጎች በቂ ግንዛቤ አግኝተው በእውቀት ላይ ተመስርተው መብታቸውን መጠቀም እንዲችሉ ድርጅቶቹ የማስተማርና የማስገንዘብ ስራ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። በዚሁ መሰረትም በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች ተሳትፎ እንዲጠናከር የሲቪክ ማህበራት የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት እየተዘጋጁ መሆኑን አንስተዋል። በባለስልጣኑ የታቀፉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ አጠቃላይ ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን እንደሚሰሩም ገልጸዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ54 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምርጫን የመታዘብ፣ እንዲሁም ህብረተሰቡን ለማስተማር ፈቃድ በመስጠቱ ምህዳሩን አስፍቶልናል ያሉት ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ታደሉ እጀታ ናቸው።   ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት ምክር ቤቱ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀቱን በመግለጽ። ለምርጫ ሂደት መሳካት የዜጎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት በቂ ግንዛቤ ኖሯቸው እንዲሳተፉ ድርጅቱ ሚናውን ይወጣል ሲሉም አክለዋል። የሲዳማ ክልል ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ማስረሻ ክብረት፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ ሂደት አወንታዊ አበርክቶ እንዲኖራቸው ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል።   በዚህም መሰረት የሲቪክ ማህበራት ሚናቸውን መወጣት የሚያስችል ዝግጁነት እንዳላቸውም ነው ጨምረው የተናገሩት። በአንድ ሀገር የምርጫ ሂደት ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሲቪክ ማህበራት ሚና የላቀ መሆኑ ይታመናል።
የጋራ ትርክት ግንባታ የሁሉንም አካላት ተሳትፎ የሚሻ ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው
Jan 13, 2026 55
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክት ግንባታ የሁሉንም አካላት ተሳትፎ የሚሻ ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ ፕሮጀክት መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አብዱላዚዝ ዳውድ(ዶ/ር) ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክትን ለመቅረጽና ተቋማዊ ለማድረግ በጅማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ ኮንፍረንስ "የጅማ ስምምነት መግለጫ" በማውጣት በስኬት ተጠናቋል።   በኮንፍረንሱ መዝጊያ ላይ ንግግር ያደረጉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አብዱላዚዝ ዳውድ(ዶ/ር)፤ መድረኩ በሀገራዊ ትርክት ዙሪያ ጥልቅ ውይይት የተደረገበትና እጅግ ውጤታማ እንደነበረ ገልጸዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ የአንድ ወቅት ተግባር ሳይሆን ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ ፕሮጀክት መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው ሂደቱ የሁሉንም አካላት ንቁ ተሳትፎ እንደሚፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል። በተለይ የሃይማኖት ተቋማት እና የሲቪክ ማኅበረሰቡ ድርሻ እጅግ ከፍተኛ መሆኑንም ነው ጨምረው የተናገሩት። በመሆኑም የስልጡን እና ሰላማዊ ፖለቲካ ማዕከል(CRPP) የጀመረውን ይህን አበረታች መድረክ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ይህ ሀገራዊ የጋራ ፕሮጀክት ከግብ እንዲደርስና ስኬታማ እንዲሆን የድርሻውን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። ለውይይቱ ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጉ አዘጋጆች፣ ምሁራንና ታዳሚዎች ምስጋና አቅርበዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ የወጣው የጅማ ስምምነት መግለጫ ኢትዮጵያውያን የሚያስተሳስሯቸውን የወል እሴቶች በማጎልበት ከፋፋይ ትርክቶችን በጋራ ለመታገልና አስተሳሳሪ ሀገራዊ ትርክት መገንባት የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን የያዘ ነው።
ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል
Jan 13, 2026 135
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ ምክክር መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የጋራ የምክክር መድረኩ የመንግሥታት ግንኙነት ስርዓትን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 1231/2013 መሰረት ይካሄዳል። በፌዴራል መንግሥት ፖሊሲዎች ሕጎችና ስትራቴጂዎች ላይ ተቀራራቢ አፈፃፀም፣ የጋራ መግባባት፣ ማሕበራዊ ፍትህ፣ ዘላቂ ሰላምና መልካም አስተዳደር፣ ዲሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብት ጥበቃ እንዲሁም አንድ የፖለቲካ ማህበረሰብ ለመገንባት ያለመ ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በዚህ ወቅት፣ ሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ ምክክር መድረክ ዘላቂ ሰላምና ልማትን በማረጋገጥ የአንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በዘንድሮው የምክክር መድረክ ወቅታዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ተነስተው ከፌደራልና ከክልል ህግ አውጪዎች ጋር ውይይት ይደረግባቸዋል ብለዋል። ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ዝግጅትና የምክር ቤቶች ሚና፣ የፐብሊክ በጀትና የፋይናንስ ትንተና እና ጥናት ሰነድ እንዲሁም የሕግ ኦዲት ሰነድ ላይ ምክክር እንደሚደረግም ገልጸዋል። መንግስት ሰባተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የግብዓት አቅርቦትና ሚና በተመለከተ ምክክር ማድረጉን ተናግረዋል።   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የክልል ምክር ቤቶች የዘንድሮው ምርጫ ከስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በተሻለ እንዲፈጸም የማስተባበር ሚናችንን በብቃት መወጣት አለብንም ነው ያሉት። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በርካታ ሪፎርሞች ማድረጉን በማንሳት፤ የክትትልና ቁጥጥር፣ የህዝብ ውክልና ሥራ በብቃት መወጣት የሚያስችል ሥራ እያከናወነ መሆኑንም አክለዋል። በዚህም ምክር ቤቱ የህግ ማዕከል በማቋቋም የሚወጡ ህጎች ከህገ መንግስቱ፣ ከዓለም አቀፍ ህጎች እና ቀድመው ከነበሩ ሀገራዊ ህጎች ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውንና ተፈፃሚነታቸውን መከታተል የሚያስችል አሰራር ተዘርግቷል ብለዋል። የሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ የምክክር መድረክ የጋራ ትርክትን መገንባትና ግልፅነትን መፍጠር የሚያስችል ምህዳር ማስፈን እንደሚያስችል ጨምረው ገልጸዋል።
የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት ነው
Jan 12, 2026 131
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት መሆኑን አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።   አምባሳደር ሌንጮ ባቲ በኮንፍረንሱ ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ የጋራ ትርክት መገንባት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ልዩነቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ በማምጣት መወያየትና መነጋገር እንደሚገባ ጠቁመው፤ ምክክር ማድረግ ሁነኛ አማራጭ ነው ብለዋል። አንድነትን፣ አብሮነትንና እኩልነትን የሚያጎላ ትርክት መቅረጽ እንደሚገባም ተናግረዋል።   የሚያስተሳስሩ እና ዘመን ተሻጋሪ አብሮነቶችና ትስስሮችን ማጉላት የሚያስችል ትርክትን መገንባት እንደሚገባም ገልጸዋል። የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመችና የበለጸገች ኢትዮጵያን መፍጠር መሆኑንም አንስተዋል።   "ሀገራዊ ማንነት፣ የጋራ ትውስታዎችና የሀገረ መንግሥት ቅቡልነት፤ የኢትዮጵያ ተሞክሮ እና የመገናኛ ብዙኃን ሚና" በሚል ርዕስ ጽሑፍ ያቀረበችው ሙኒራ አብዱልመናን መገናኛ ብዙኃን የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በማሳለጥና የዜጎችን የጋራ ማንነት በመቅረጽ ረገድ የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ተናግራለች። መገናኛ ብዙሃን ከአግላይና ነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ የወል ትርክቶችን እና እሴቶችን ማጉላት እና ማስተጋባት እንደሚገባቸው ገልጻለች። መገናኛ ብዙኃን ለብሔራዊ መግባባት ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባም ጨምራ ተናግራለች። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችም ስለ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸው ግንዛቤ ሊያድግ እንደሚገባ በመግለጽ፤ ለትውልድ የሚሻገር አስተሳሳሪ ትርክት ለመገንባት መትጋት እንደሚገባቸውም አንስታለች። በመድረኩ በኢትዮጵያ የጋራ ትርክትን ተቋማዊ ለማድረግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ሰፊ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Jan 12, 2026 106
ጋምቤላ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። የጋምቤላ ክልል የመንግስት ሰራተኞች በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ የውይይት መድረክ አካሂደዋል። በውይይት መድረኩ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ፤ በክልሉ የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት የመንግስት ሰራተኞች ተሳትፎ እና ትብብር ወሳኝ መሆኑን አንስተው በሁሉም ረገድ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠልና የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የሚነጣጥሉ እሳቤዎችን በመተው አሰባሳቢና የወል ትርክቶችን በመገንባት ረገድም የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ የሚጥሩ አካላትን በመከታተል በህግ ተጠያቂ የማድረግ፣ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥና የልማት ስራዎችን ለስኬት የማብቃት ጉዳይ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ይሰራል ብለዋል።   የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) የክልሉ መንግስት የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ የልማት ስራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም የሁሉም ድጋፍና ትብብር አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በተለይም የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ አስገንዝበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን፤ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በማጠናከር ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ልንቆም ይገባል ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች መሳካት የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በጋምቤላ ክልል ለልማት የሚውል እምቅ የተፈጥሮ ሀብት መኖሩን አንስተው በጋራ በመስራትና በማልማት ጥቅም ላይ የማዋል ስራ እንዲሳካ እንሰራለን ብለዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የጋራ ትርክት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ለትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና አለው
Jan 12, 2026 134
አዲስ አበባ፤ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የጋራ ትርክት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና እንዳለው የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ብሔራዊ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በኮንፍረንሱ ታዋቂው የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ "የጋራ የወል ትርክት ግንባታ እና ፈተናዎቹ" በሚል ርዕስ የመነሻ ጽሑፍ አቅርበዋል።   በመነሻ ጽሑፋቸውም፤ ኢትዮጵያዊያን ከልዩነትና ነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ በጋራ ትርክት ላይ በማተኮር ለጽኑ ሀገረ መንግሥት ግንባታ በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። አግላይና ነጣጣይ ትርክት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ፈታኝ መሆናቸውን በመጥቀስ የዜጎችን አንድነትና አብሮነት የሚያጠናክር የወል ትርክት መፍጠር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ የወል ትርክት ግንባታም በታሪክ ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ ስብራቶችን በሚያርቅ አካሄድ አብሮነትን በሚያጸኑና ሁሉንም ወገኖች በሚያቅፉ የታሪክ እውነታዎች ላይ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል። ምሁራን ታሪክን ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕዝቦች መቀራረብ እንዲውል የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።   የጋራ ትርክት ግንባታ ሂደቱንም በተሻለ የሃሳብ የበላይነት በመምራትም የተሻለችና አስተሳሳሪ ትርክት የነገሰባት ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ለተሻለ የትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አብራርተዋል። በኮንፍረንሱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማን እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።  
ፖለቲካ
በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል
Jan 13, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ ምክክር መድረክ በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ እና በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እየተካሄደ ነው።   በመርሀ ግብሩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ ምክትል አፈ ጉባዔ ሎሚ በዶ፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር)፣ የክልሎች አፈ ጉባኤዎችና ምክትል አፈ ጉባኤዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ "የሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ዝግጅትና የምክር ቤቶች ሚና" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል። ምክትል ሰብሳቢው በገለፃቸው፤ ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የመራጮች ምዝገባ እንዲከናወን እና የድምፅ መስጫው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሆን ቦርዱ መወሰኑን አስታውቀዋል።   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይሄንን ታሳቢ በማድረግ የግብዓት ማሟላት፣ የስልጠናና ግንዛቤ የመፍጠሪያ የተለያዩ ዝግጅቶችን ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም ቦርዱ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ከመደበኛ የምርጫ ጣቢያዎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ በሥራ ምክንያት በተለያየ ቦታ የሚገኙ ዜጎች፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና ሌሎች ልዩ የምርጫ ጣቢያ ሊቋቋምላቸው የሚገባ ስለሆነ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር መስራታቸውን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ50 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚኖሩ የገለጹት ምክትል ሰብሳቢው፤ በአዋጁ መሰረት እያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ ከ 1 ሺህ 500 የማይበልጥ መራጭ መያዝ አለበት ብለዋል። በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት የምርጫ ስራዎችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ለቦርዱ አቅም የሚፈጥሩ ድንጋጌዎች መካተታቸውን ገልጸዋል። በዚህም የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባ እንዲሁም ሌሎች የቦርዱን ስራ ውጤታማ ሊያደርጉ የሚችሉና የቅሬታ አፈታት ስልቶች ማሻሻያ እንደተደረገባቸው ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ቦርዱ በኢትዮጵያ በየትኛውም አካባቢ ምርጫውን ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት ማድረጉን ተናግረዋል። መራጮች በዲጂታል ወይም በአካል በመቅረብ መመዝገብ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መተግበሪያ አማካኝነት ባሉበት ሆነው መመዝገብ የሚፈልጉ መራጮች የብሔራዊ መታወቂያ ሊኖራቸው እንደሚገባ ገልጸዋል። በቦርዱ የተመለመሉ የምርጫ አስፈፃሚዎች ከማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ገለልተኛ የሆኑ ለስራው በቂ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውና የአካባቢውን የስራ ቋንቋና ባህል የሚያውቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።በመላ ሀገሪቱ ቢያንስ 318 ሺህ ምርጫ አስፈፃሚ እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡ የፖለቲካ ፖርቲዎች የፅሁፍና የቃል ፈተናውን ያለፉ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ገለልተኝነት በተመለከተ አስተያየት እንዲሰጡ ተደርጓል ብለዋል።
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች ተሳትፎ እንዲጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት እየተዘጋጁ ነው
Jan 13, 2026 74
ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በግንቦት ወር ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች ተሳትፎ እንዲጠናከር የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት እየተዘጋጁ መሆኑን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጠቅላላ ምርጫው ሂደት ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ ከወዲሁ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ለምርጫው ሂደት የቦርዱ የተሟላ ዝግጅት እንዳለ ሆኖ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትና አጠቃላይ የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎ ወሳኝ ነው። በዚህም መሰረት የዜጎች የምርጫ ተሳትፎ እንዲጠናከር በማድረግ በኩል በተለይም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዝግጁነት ምን ይመስላል ሲል ኢዜአ የሚለከታቸው አካላትን አነጋግሯል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ፤ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሂደት ሁነኛ መሰረት በሆነው የምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ሂደትም ዜጎች በቂ ግንዛቤ አግኝተው በእውቀት ላይ ተመስርተው መብታቸውን መጠቀም እንዲችሉ ድርጅቶቹ የማስተማርና የማስገንዘብ ስራ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። በዚሁ መሰረትም በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች ተሳትፎ እንዲጠናከር የሲቪክ ማህበራት የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት እየተዘጋጁ መሆኑን አንስተዋል። በባለስልጣኑ የታቀፉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ አጠቃላይ ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን እንደሚሰሩም ገልጸዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ54 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምርጫን የመታዘብ፣ እንዲሁም ህብረተሰቡን ለማስተማር ፈቃድ በመስጠቱ ምህዳሩን አስፍቶልናል ያሉት ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ታደሉ እጀታ ናቸው።   ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት ምክር ቤቱ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀቱን በመግለጽ። ለምርጫ ሂደት መሳካት የዜጎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት በቂ ግንዛቤ ኖሯቸው እንዲሳተፉ ድርጅቱ ሚናውን ይወጣል ሲሉም አክለዋል። የሲዳማ ክልል ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ማስረሻ ክብረት፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ ሂደት አወንታዊ አበርክቶ እንዲኖራቸው ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል።   በዚህም መሰረት የሲቪክ ማህበራት ሚናቸውን መወጣት የሚያስችል ዝግጁነት እንዳላቸውም ነው ጨምረው የተናገሩት። በአንድ ሀገር የምርጫ ሂደት ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሲቪክ ማህበራት ሚና የላቀ መሆኑ ይታመናል።
የጋራ ትርክት ግንባታ የሁሉንም አካላት ተሳትፎ የሚሻ ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው
Jan 13, 2026 55
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክት ግንባታ የሁሉንም አካላት ተሳትፎ የሚሻ ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ ፕሮጀክት መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አብዱላዚዝ ዳውድ(ዶ/ር) ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክትን ለመቅረጽና ተቋማዊ ለማድረግ በጅማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ ኮንፍረንስ "የጅማ ስምምነት መግለጫ" በማውጣት በስኬት ተጠናቋል።   በኮንፍረንሱ መዝጊያ ላይ ንግግር ያደረጉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አብዱላዚዝ ዳውድ(ዶ/ር)፤ መድረኩ በሀገራዊ ትርክት ዙሪያ ጥልቅ ውይይት የተደረገበትና እጅግ ውጤታማ እንደነበረ ገልጸዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ የአንድ ወቅት ተግባር ሳይሆን ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ ፕሮጀክት መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው ሂደቱ የሁሉንም አካላት ንቁ ተሳትፎ እንደሚፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል። በተለይ የሃይማኖት ተቋማት እና የሲቪክ ማኅበረሰቡ ድርሻ እጅግ ከፍተኛ መሆኑንም ነው ጨምረው የተናገሩት። በመሆኑም የስልጡን እና ሰላማዊ ፖለቲካ ማዕከል(CRPP) የጀመረውን ይህን አበረታች መድረክ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ይህ ሀገራዊ የጋራ ፕሮጀክት ከግብ እንዲደርስና ስኬታማ እንዲሆን የድርሻውን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። ለውይይቱ ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጉ አዘጋጆች፣ ምሁራንና ታዳሚዎች ምስጋና አቅርበዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ የወጣው የጅማ ስምምነት መግለጫ ኢትዮጵያውያን የሚያስተሳስሯቸውን የወል እሴቶች በማጎልበት ከፋፋይ ትርክቶችን በጋራ ለመታገልና አስተሳሳሪ ሀገራዊ ትርክት መገንባት የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን የያዘ ነው።
ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል
Jan 13, 2026 135
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ማከናወን የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ ምክክር መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የጋራ የምክክር መድረኩ የመንግሥታት ግንኙነት ስርዓትን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 1231/2013 መሰረት ይካሄዳል። በፌዴራል መንግሥት ፖሊሲዎች ሕጎችና ስትራቴጂዎች ላይ ተቀራራቢ አፈፃፀም፣ የጋራ መግባባት፣ ማሕበራዊ ፍትህ፣ ዘላቂ ሰላምና መልካም አስተዳደር፣ ዲሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብት ጥበቃ እንዲሁም አንድ የፖለቲካ ማህበረሰብ ለመገንባት ያለመ ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በዚህ ወቅት፣ ሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ ምክክር መድረክ ዘላቂ ሰላምና ልማትን በማረጋገጥ የአንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በዘንድሮው የምክክር መድረክ ወቅታዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ተነስተው ከፌደራልና ከክልል ህግ አውጪዎች ጋር ውይይት ይደረግባቸዋል ብለዋል። ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ዝግጅትና የምክር ቤቶች ሚና፣ የፐብሊክ በጀትና የፋይናንስ ትንተና እና ጥናት ሰነድ እንዲሁም የሕግ ኦዲት ሰነድ ላይ ምክክር እንደሚደረግም ገልጸዋል። መንግስት ሰባተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የግብዓት አቅርቦትና ሚና በተመለከተ ምክክር ማድረጉን ተናግረዋል።   የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የክልል ምክር ቤቶች የዘንድሮው ምርጫ ከስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በተሻለ እንዲፈጸም የማስተባበር ሚናችንን በብቃት መወጣት አለብንም ነው ያሉት። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በርካታ ሪፎርሞች ማድረጉን በማንሳት፤ የክትትልና ቁጥጥር፣ የህዝብ ውክልና ሥራ በብቃት መወጣት የሚያስችል ሥራ እያከናወነ መሆኑንም አክለዋል። በዚህም ምክር ቤቱ የህግ ማዕከል በማቋቋም የሚወጡ ህጎች ከህገ መንግስቱ፣ ከዓለም አቀፍ ህጎች እና ቀድመው ከነበሩ ሀገራዊ ህጎች ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውንና ተፈፃሚነታቸውን መከታተል የሚያስችል አሰራር ተዘርግቷል ብለዋል። የሀገር አቀፍ የሕግ አውጪዎች የጋራ የምክክር መድረክ የጋራ ትርክትን መገንባትና ግልፅነትን መፍጠር የሚያስችል ምህዳር ማስፈን እንደሚያስችል ጨምረው ገልጸዋል።
የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት ነው
Jan 12, 2026 131
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመች ሀገር መፍጠር ማለት መሆኑን አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።   አምባሳደር ሌንጮ ባቲ በኮንፍረንሱ ባቀረቡት የመወያያ ጽሑፍ የጋራ ትርክት መገንባት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ልዩነቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ በማምጣት መወያየትና መነጋገር እንደሚገባ ጠቁመው፤ ምክክር ማድረግ ሁነኛ አማራጭ ነው ብለዋል። አንድነትን፣ አብሮነትንና እኩልነትን የሚያጎላ ትርክት መቅረጽ እንደሚገባም ተናግረዋል።   የሚያስተሳስሩ እና ዘመን ተሻጋሪ አብሮነቶችና ትስስሮችን ማጉላት የሚያስችል ትርክትን መገንባት እንደሚገባም ገልጸዋል። የጋራ ትርክት መገንባት ለነገው ትውልድ የምትመችና የበለጸገች ኢትዮጵያን መፍጠር መሆኑንም አንስተዋል።   "ሀገራዊ ማንነት፣ የጋራ ትውስታዎችና የሀገረ መንግሥት ቅቡልነት፤ የኢትዮጵያ ተሞክሮ እና የመገናኛ ብዙኃን ሚና" በሚል ርዕስ ጽሑፍ ያቀረበችው ሙኒራ አብዱልመናን መገናኛ ብዙኃን የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በማሳለጥና የዜጎችን የጋራ ማንነት በመቅረጽ ረገድ የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ተናግራለች። መገናኛ ብዙሃን ከአግላይና ነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ የወል ትርክቶችን እና እሴቶችን ማጉላት እና ማስተጋባት እንደሚገባቸው ገልጻለች። መገናኛ ብዙኃን ለብሔራዊ መግባባት ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባም ጨምራ ተናግራለች። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችም ስለ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸው ግንዛቤ ሊያድግ እንደሚገባ በመግለጽ፤ ለትውልድ የሚሻገር አስተሳሳሪ ትርክት ለመገንባት መትጋት እንደሚገባቸውም አንስታለች። በመድረኩ በኢትዮጵያ የጋራ ትርክትን ተቋማዊ ለማድረግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ሰፊ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Jan 12, 2026 106
ጋምቤላ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። የጋምቤላ ክልል የመንግስት ሰራተኞች በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ የውይይት መድረክ አካሂደዋል። በውይይት መድረኩ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ፤ በክልሉ የህግ የበላይነትን በማስከበር የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት የመንግስት ሰራተኞች ተሳትፎ እና ትብብር ወሳኝ መሆኑን አንስተው በሁሉም ረገድ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠልና የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የሚነጣጥሉ እሳቤዎችን በመተው አሰባሳቢና የወል ትርክቶችን በመገንባት ረገድም የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ የሚጥሩ አካላትን በመከታተል በህግ ተጠያቂ የማድረግ፣ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥና የልማት ስራዎችን ለስኬት የማብቃት ጉዳይ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ይሰራል ብለዋል።   የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) የክልሉ መንግስት የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ የልማት ስራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም የሁሉም ድጋፍና ትብብር አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በተለይም የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ አስገንዝበዋል። በብልፅግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን፤ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በማጠናከር ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ልንቆም ይገባል ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችም ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች መሳካት የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በጋምቤላ ክልል ለልማት የሚውል እምቅ የተፈጥሮ ሀብት መኖሩን አንስተው በጋራ በመስራትና በማልማት ጥቅም ላይ የማዋል ስራ እንዲሳካ እንሰራለን ብለዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የጋራ ትርክት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ለትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና አለው
Jan 12, 2026 134
አዲስ አበባ፤ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦የጋራ ትርክት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና እንዳለው የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ብሔራዊ ኮንፍረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በኮንፍረንሱ ታዋቂው የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ "የጋራ የወል ትርክት ግንባታ እና ፈተናዎቹ" በሚል ርዕስ የመነሻ ጽሑፍ አቅርበዋል።   በመነሻ ጽሑፋቸውም፤ ኢትዮጵያዊያን ከልዩነትና ነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ በጋራ ትርክት ላይ በማተኮር ለጽኑ ሀገረ መንግሥት ግንባታ በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። አግላይና ነጣጣይ ትርክት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ፈታኝ መሆናቸውን በመጥቀስ የዜጎችን አንድነትና አብሮነት የሚያጠናክር የወል ትርክት መፍጠር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ የወል ትርክት ግንባታም በታሪክ ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ ስብራቶችን በሚያርቅ አካሄድ አብሮነትን በሚያጸኑና ሁሉንም ወገኖች በሚያቅፉ የታሪክ እውነታዎች ላይ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል። ምሁራን ታሪክን ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕዝቦች መቀራረብ እንዲውል የማድረግ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።   የጋራ ትርክት ግንባታ ሂደቱንም በተሻለ የሃሳብ የበላይነት በመምራትም የተሻለችና አስተሳሳሪ ትርክት የነገሰባት ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ለተሻለ የትውልድ ሽግግር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አብራርተዋል። በኮንፍረንሱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማን እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።  
ማህበራዊ
የውጭ ሃገራት ፍልሰት በህጋዊ ሥርዓት እንዲመራ የተሰራው ሥራ ውጤት እያመጣ ነው 
Jan 13, 2026 70
ሆሳዕና፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦የዜጎችን ሰብአዊ መብትና ክብርን ለማስጠበቅ የውጭ ሃገራት ፍልሰት በህጋዊ ሥርዓት እንዲመራ የተሰራው ሥራ ውጤት እያመጣ መሆኑን የፍትህ ሚኒስቴር ገለፀ። በሰው የመነገድ ወንጀልን በመከላከልና በዳያስፖራ ተሳትፎ ላይ የሚመክር የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው። በዚህ ወቅት የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ እንዳሉት፤ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ተለያዩ ሃገራት በፍልሰት የሚሄዱ ዜጎች ሰብአዊ መብታቸውና ክብራቸው ተነክቶ ለእንግልት እና ለሞት እየተዳረጉ ነው።   ችግሩን ለመከላከልና ለመቀነስ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፍ አዋጆችን ከመተግበር ባለፈ በሀገሪቱ በአዲስ መልክ ብሔራዊ ምክር ቤት እና የትብብር ጥምረት ጽህፈት ቤት ተቋቁሞ በቅንጅት በተሰራው ሥራ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል። ከዚህ ጎን ለጎን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሥራ ዕድሎችን በማስፋት የዜጎች ፍልሰት ጫናን ለመቀነስ መቻሉን አውስተዋል። ከስደት ተመላሽ ዜጎችን የማቋቋም ሥራ ትኩረት እንደተሰጠው በመጠቆም ወንጀል ፈጽመው በተለያዩ ሃገራት የሚገኙ ዜጎች ከሚገኙበት ሀገራት ጋር በመቀናጀት ተጠያቂ የማድረግ ሥራም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍፁም አረጋ፤ በርካታ ዜጎች በህገ ወጥ ደላሎች ተታለው ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ከዚያም ባለፈ ለህልፈት እየተዳረጉ መሆናቸውን ገልጸው፣ እነዚህን ዜጎች ለመታደግ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።   ለስደት ገፊ ምክንያቶችን በመለየት በሃገር ውስጥ እና በተለያዩ ሃገራት በህጋዊ መንገድ የሥራ ባለቤት እንዲሆኑ እየተሰራ ያለውን ሥራም በማሳያነት ጠቅሰዋል። ከተለያዩ ሀገራት ጋር የጋራ ቅንጅት በመፍጠር የህገ ወጥ ስደት አሳሳቢነት ከማስገንዘብ ባለፈ በችግር ውስጥ ያሉ ዜጎችን ወደ ሃገር ውስጥ የመመለስ ሥራም ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የዳያስፖራው ተሳትፎ እያደገ መሆኑንም ገልጸዋል።   በህጋዊ መንገድ የሚላክን ገንዘብ ለማሳደግ በተሰራው ሥራም በተያዘው በጀት ዓመት ግማሽ ዓመት ህጋዊ የገንዘብ ዝውውሩ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተናግረዋል። በርካታ ዳያስፖራዎች በሀገር ውስጥ በኢንቨስትመንት ዘርፍ እንዲሳተፉ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም መዋዕለንዋያቸውን በማፍሰስ ለዜጎችም የሥራ ዕድል እየፈጠሩ መሆኑን አስረድተዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ በበኩላቸው፤ በክልሉ በሰው የመነገድ ወንጀል የሚሳተፉ ዜጎችን ተጠያቂ የማድረግ ሥራ እየተሰራ ነው።   በተለያየ ምክንያት ተታለው በህገ ወጥ መንገድ ወደውጭ ሀገር የሚሄዱትን ከመከላከል ባለፈ ዜጎች ለሥራ ወደውጭ ሲሄዱ ህጋዊ አሰራርን እንዲከተሉ የማስገንዘብ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል ። እንደእሳቸው ገለጻ፤ ከህገወጥ ፍልሰት ጋር በተያያዘ የሚታየውን ችግር ለመቀነስ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ሥራ እየተሰራ ነው። ለሁለት ቀናት እየተካሄደ ባለው የምክክር መድረክ የፌደራልና የክልሉ የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች፣ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የስደት ተመላሾችና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በመሳተፍ ላይ ናቸው። በተጨማሪም በደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ፣ ዚምባብዌና ታንዛንያ የሚገኙ የኢትዮጵያ አምባሳደሮች በቨርችዋል እየተሳተፉ ነው።
መንግስት የመንግስት ሠራተኞችን የቤት ችግር ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ
Jan 13, 2026 34
ግራዋ ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦የክልሉ መንግስት የመንግስት ሠራተኞችን የቤት ችግር ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ሲሉ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አሰፋ ገለጹ፡፡ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የግራዋ ከተማ አስተዳደር በማህበር ለተደራጁ 336 የመንግስት ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ሰጥቷል። የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አሰፋ በቦታ ርክክብ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ የክልሉ መንግስት የመንግስት ሠራተኞችን የቤት ችግር ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።   ለመንግስት ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ መሰጠቱ ሠራተኛው የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ በማድረግ በስራው ላይ ፍትሐዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችለዋል ብለዋል። የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ሚስኪ መሐመድ በበኩላቸው፤ ለሠራተኞቹ የተሰጣቸው መሬት ከመኖሪያ ቤት ጋር በተያያዘ ሲነሱ የነበሩ የዜጎች ጥያቄን የሚያቃልል መሆኑን አመልክተዋል። የሠራተኞች የቤት ጥያቄ መፈታት በተሰማሩበት መስክ ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ለማሻሻል ያግዛል ነው ያሉት።   በዛሬው እለት የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ የተሰጣቸው መምህራን፣ የጤና ባለሙያዎች፣ የፀጥታና የፍትህ አካላት ሲሆኑ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ በማግኘታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል። በዚህም ከመንግስት ጋር በጋራ በመሆን ልማትን እንደሚያፋጥኑ ገልጸው፣ በተሰማሩበት ሥራ ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ ዘርፉን በኢኖቬሽን የመደገፍ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jan 13, 2026 45
ቢሾፍቱ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ ዘርፉን በኢኖቬሽን የመደገፍ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ ገለፁ። ሀገር አቀፍ የጤና አገልግሎት ጥራት እና ኢኖቬሽን ጉባኤ በኦሮሚያ ጤና ቢሮ አዘጋጅነት በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ነው።   የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ በመድረኩ እንደተናገሩት፤ የጤና አገልግሎት ጥራትን በማሻሻል ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከል ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። የጤና አገልግሎት ጥራቱን ለማሻሻል ኢኖቬሽንና ዲጂታላይዜሽን ላይ በስፋት በመስራት ፍትሃዊ ተደራሽነቱን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል። የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ኃላፊ ፕሮፌሰር ነጻነት ወርቅነህ በበኩላቸው፤ በክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ለዲጂታላይዜሽን፣ ለሰው ሃይል አቅም ግንባታና የሕክምና ግብአት ማሟላት ላይ በሰፊው መሰራቱን አንስተዋል።   የጤና አገልግሎት ጥራት ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍና አዳዲስ ፈጠራዎችን ወደ ስራ በማስገባት የተገልጋዩን እርካታ እውን ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። በጤና አገልግሎት ጥራት ፍትሃዊነትና ተደራሽነት ላይ የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል የጤና ኢኖቬሽን ስራዎችን ባህል ማድረግና ትብብሩን ማጠናከር እንደሚገባም ተናግረዋል። የጤናው ዘርፍ የኢኖቬሽን ስራዎችን የሚያሳዩ ኤግዚቢሽኖች፣ ጥናትና ምርምሮች እንዲሁም ትብብርን የሚያጠናክሩ ውይይቶችና ሌሎች ሁነቶች በጉባኤው ይካሄዳሉ ብለዋል። በጉባኤው ላይ የፌዴራልና የክልል አመራሮች፣ የዓለም ጤና ድርጅትና ዩኒሴፍ ተወካዮች፣ የምርምር ተቋማት፣ የግሉ ሴክተር እና ግብረሰናይ ድርጅቶች ተሳትፈዋል።
የሃይማኖት አባቶች የክልሉን ሰላም ለማጽናት ሊተጉ ይገባል
Jan 13, 2026 44
ጋምቤላ ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦የሃይማኖት አባቶች በማህበረሰቡ ዘንድ ያላቸውን ተደማጭነት በመጠቀም የክልሉን ሰላም ለማጽናት ሊተጉ እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለፁ። በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሃይማኖት አባቶች ጋር የውይይት መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል። ርዕሰ መስተዳድሯ በመድረኩ ላይ እንዳሉት የሃይማኖት አባቶች ሰላምን በመገንባት ረገድ ያላቸው ሚና ከፍተኛ ነው።   መንግስት በክልሉ በሚያከናውናቸው የሰላም ግንባታ ስራዎች ላይ የሃይማኖት አባቶች አስተዋጽኦ የላቀ በመሆኑ መድረኩ መዘጋጀቱንም ተናግረዋል። ለግጭት መንስኤ የሚሆኑ የአመለካከት፣ የአስተሳሰብና የነጠላ ትርክትን በመግራት በኩል የሃይማኖት አባቶች በማህበረሰቡ ዘንድ ያላቸውን ተሰሚነት ተጠቅመው ለክልሉ ሰላም ሊተጉ እንደሚገባ ገልፀዋል።   በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና የህዝቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የሰላም ግንባታ ስራዎቻችንን አጠናክረን ልንቀጥል ይገባል ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሯ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ በክልሉ የተገኘውን ሰላም ይበልጥ ለማጽናት በሚደረገው ጥረት የሃይማኖት አባቶች እገዛ ሊጠናከር ይገባል።   በተለይም የሃይማኖት አባቶች የጋራ የሆኑ እሴቶችን በማስተማር ለክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት የበኩላቸውን አበርክቶ እንዲወጡ አስገንዝበዋል። በመከላከያ ሰራዊት የዳሎል ማዕከላዊ እዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀነራል ሙላቱ ጀልዱ በበኩላቸው ፤ትውልድን በስነ-ምግባር በማነጽ ረገድ የሃይማኖት ተቋማት የጎላ ሚና አላቸው ብለዋል።   በመሆኑም የእምነት አባቶች ህዝቡን ስለ ሰላም በማስተማር የክልሉን ሰላም ይበልጥ ለማጽናት መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የውይይት መድረኩ ተሳታፊ የሃይማኖት አባቶች የክልሉን ሰላም ለማጽናት ከመንግስት ጎን በመሆን የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። በተለይም በየእምነት ተቋማቱ ማህበረሰቡን በመልካም ስነ-ምግባር በማነጽና ሰላምን በማስፈን ረገድ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ገልፀዋል።
ኢኮኖሚ
በከተማና ገጠር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሠረተ ልማቶች ለውጤት እየበቁ ነው
Jan 13, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦በከተማና ገጠር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሠረተ ልማቶች ለውጤት እየበቁ መሆናቸውን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ። በሀገር አቀፍ ደረጃ በ 76 ከተሞች ውጤታማ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የተገነባውን የመኖሪያ መንደርና ሌሎች የከተማና ገጠር የልማቶችን በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ በጥቂት ዓመታት ውስጥ በከተማና ገጠር ሰው ተኮር የልማት ሥራ ከተሞችን በማስዋብ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ሰፋፊ የልማት ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል። ለአብነትም በአማራ ክልል ሰቆጣ ከተማ፣ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ እንዲሁም ሐረር ከተማን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ መኖሪያ ቤቶች መገንባታቸውን አስታውቀዋል። በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብርም በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የቱሉ አራራ የተቀናጀ ሞዴል መንደር ተገንብቶ ለህዝብ ክፍት መደረጉን ተናግረዋል። የአዲስ አበባን ውጤታማ የኮሪደር ልማት በምሳሌነት በመውሰድ በ76 ከተሞች የሚገነባው የኮሪደር ልማት ሥራም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን አንስተዋል። የከተሞች የኮሪደር ልማትም በሥራ ዕድል ፈጠራና በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከሚፈጥሩት አቅም ባሻገር በከተሞች መካከል ጤናማ ውድድር እንዲኖር እያደረገ መሆኑን አብራርተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በከተማና ገጠር የሚገነቡ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የኢትዮጵያን የተሟላ ብልጽግና ማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውንም አስረድተዋል።
በዞኑ አርሶ አደሮች የሩዝ ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚ ሆነዋል
Jan 13, 2026 53
ጎንደር ፤ጥር 5/2018 ( ኢዜአ) ፡-በማእከላዊ ጎንደር ዞን አርሶ አደሮች የሩዝ ምርታማነትን በማሳደግ ከምግብ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸው ተመለከተ። የዞኑ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ የመጣው የሩዝ ልማት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እያስቻለ ነው። በዚህም በዘንድሮው መኸር በአምስት ወረዳዎች በ44ሺ ሄክታር መሬት ላይ ከለማ ሩዝ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን ገልጸዋል። አርሶአደሩ እያገኘ ባለው ከፍተኛ የሩዝ ምርት ከራሱ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ዘላቂ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ መምጣቱን አስረድተዋል። በምርምር የወጡ የሩዝ ዝርያዎችን በኩታ ገጠምና በመስመር በመዝራት እንዲሁም ሌሎች ቴክኖሎጅዎችን በመጠቀም በፊት በሄክታር ይገኝ የነበረውን 20 ኩንታል አማካይ ምርት በእጥፍ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በአርሶ አደሩ ዘንድ ሩዝ ዋነኛ የምግብ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን የጠቆሙት ሃላፊው ለቅንጨ፣ ለእንጀራ ለዳቦና ለቂጣ በስፋት ለምግብነት እየዋለ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ የሮቢት ቀበሌ ነዋሪ አርሶአደር ሙሉቀን ታምራት እንዳሉት ዘንድሮ በግማሽ ሄክታር መሬት ላይ ካለሙት ሩዝ 20 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ ያገኙትን የሩዝ ምርት ግማሹን ለቤት ውስጥ ፍጆታ ግማሹን ደግሞ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ገልጸው ሩዝ የቤተሰባቸው ዋነኛ የምግብ ምንጭ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ የጎንደር ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አርሶአደር ታከለ ጎሼ በበኩላቸው በኩታ ገጠም ማሳ ላይ ካለሙት ሩዝ 25 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ ሩዝ ዋነኛ የቤተሰባቸው የምግብ ምንጭ ከመሆን ባለፈ በተሻለ ዋጋ ለገበያ በማቅረብ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸወንም ገልጸዋል፡፡ በማእከላዊ ጎንደር ዞን ለሩዝ ልማት ተስማሚ ከሆኑ ወረዳዎች መካከል ጎንደር ዙሪያ፣ ምስራቅና ምእራብ ደንቢያና አለፋ ወረዳዎች ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ናቸው፡፡  
በጉጂ ዞን ለአምራችና አገልግሎት ሰጭ ኢንተርፕራይዞች ከ348 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር ተፈጥሯል
Jan 13, 2026 45
አዶላ፤ ጥር 5/2018 (ኢዜአ)፡- በጉጂ ዞን ባለፉት ስድስት ወራት ለኢንተርፕራይዞች ከ348 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር መመቻቸቱን የዞኑ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ገለጸ። በጽህፈት ቤቱ የስራ እድል ፈጠራ ባለሙያ አቶ ቢራራ ገመዳ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ ባለፉት ስድስት ወራት በግብርና፣ በጎጆ ኢንደስትሪ፣ በግንባታና በአገልግሎት መስክ ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ተመቻችቷል። ኢንተርፕራይዞቹ የወተት፣ ስጋ፣ እንቁላል እንዲሁም የንብ ቆፎ፣ የቤትና የቢሮ እቃዎችንና ሌሎችንም በማምረት ለገበያ ማቅረባቸውን አመልክተዋል፡፡ የኢንተርፕራይዞችን ውጤታማነት ለማሳደግም ለ537 አምራችና አገልግሎት ሰጭ ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል፡፡ ለኢንተርፕራይዞቹ ከ348 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር መፈጠሩን ጠቁመው የገበያ ትስስሩም ከማህበራት፣ ከመንግስት ሴክተር መስሪያ ቤቶች፣ ከግብርና፣ ከጤናና ከሌሎችም የልማት ድርጅቶች ጋር የተፈጠረ መሆኑን አመልክተዋል ። በዞኑ አዶላ ከተማ የገበያ ትስስር ከተመቻቸላቸው ኢንተርፕራይዞች መካከል ቢሊሴ ቁምነገር የዘመናዊ ቀፎ ማምረቻ አንዱ ነው፡፡ የኢንተርፕራይዙ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ መና በገበያ ትስስሩ ምርታቸውን በብዛትና በጥራት በማቅረብ ገቢያቸውን ማሳደግ እንደቻሉ ጠቁመዋል፡፡ መንግስት የፈጠረላቸውን የገበያ ትስስር በመጠቀም ዘመናዊ ቀፎዎችን በብዛት በማምረት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ እስካሁን ለአዶላ ከተማ አስተዳደር፣ ለግርጃ እና ለአናሶራ ወረዳ አስተዳደሮች 240 ዘመናዊ የንብ ቀፎ በተመጣጣኝ ዋጋ በማስረከብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ከዚህ በተጨማሪም ለመንግስት ሴክተር መስሪያ ቤት ካቀረቡት ዘመናዊ ቀፎ ሽያጭ ከ360 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። በኦዶላ ከተማ የገዱፋ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ደስታ ግርማ በበኩሏ ከዩኒቨርሲቲ ከተመረቀች በኋላ ከአምስት ጓደኞቿ ጋር በመደራጀት መንግሥት ባመቻቸላቸው የመስሪያ ቦታና የብድር አገልግሎት የጣውላ መሰንጠቂያ ኢንተርፕራይዝ በመክፈት ወደ ስራ ገብተዋል። ስራውን ለማሳደግም ከመንግስት የሙያ ማሻሻያና የሂሳብ አያያዝ ስልጠና በማግኘት ጠንክረው በመስራት ሀብት ለማፍራት እየተጉ መሆናቸውን ተናግራለች። የገበያ ትስስር መፈጠሩ ምርትና አገልግሎትን በጥራት እና በብዛት በማምረት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው አስረድታለች።  
በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ8 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ እንዲገቡ ውሳኔ ተሰጥቷል
Jan 13, 2026 60
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በግማሽ ዓመቱ ከ262 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ከ8 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ እንዲገቡ ውሳኔ ማግኘታቸውን የክልሉ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ገለጸ። በዘርፉ ለመሰማራት ጥያቄ ላቀረቡ አካላት የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ የሰጠውን ውሳኔን አስመልክቶ የክልሉ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አህመድ ኢድሪስ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በክልሉ ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን ጨምሮ ከተሞችም ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እንቅስቃሴያቸውን እንዲያጠናክሩ የተደረገ ሲሆን፤ በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አማካኝነትም የኢንቨስትመንት አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ጥያቄ ላቀረቡ አካላት የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ በሁለት ዙር ውሳኔ መስጠቱን ገልጸዋል። የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ በጥቅምት ወር ባካሄደው የመጀመሪያ ዙር ስብሰባ ከ90 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 3ሺህ 163 ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ውሳኔ እንዲያገኙ አድርጓል። ፕሮጀክቶቹ በአሁኑ ወቅት አብዛኞቹ ህጋዊ ሂደቶችን አጠናቀው ስራ የጀመሩ ሲሆን በሙሉ አቅም ወደ ስራ ሲገቡ ከ200 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ ቦርዱ በታህሳስ ወር መጨረሻ ላይ ባካሄደው ስብሰባ 172 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 5ሺህ 158 ፕሮጀክቶች ፍቃድ እንዲሰጥ መወሰኑን ገልጸዋል። እነዚህ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በ45 ቀናት ውስጥ ህጋዊ ሂደቶችን አጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ እንደሚደረግ ገልጸው ፕሮጀክቶቹ በሙሉ አቅማቸው ስራ ሲጀምሩ ከ400ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ያስገኛሉ ብለዋል። በአጠቃላይ በግማሽ ዓመቱ ከ262 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ከ8ሺህ በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ፈቃድ ማግኘታቸውን አስረድተዋል። ወደ ኢንቨስትመንት እንዲገቡ የተወሰነው የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት፣ የሀገር ውስጥ ባለህብቶች፣ የተሻለ ሀብት ያፈሩ አርሶ አደሮች፣ በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ተሰማርተው ሀብት ያፈሩ ወጣቶች እንዲሁም የህብረት ስራ ማህበራት መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህ ፕሮጀክቶች ፈጥነው በሙሉ አቅም ወደ ስራ መግባት እንዲችሉ የመሬት እና ፋይናንስ አቅርቦት፣ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እና የሰለጠነ የሰው ሃይል የማቅረብ ስራ በቢሮው አማካኝነት እንደሚከናወንም አስረድተዋል። የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶቹ በአማዛኙ ተኪ ምርቶች ላይ አተኩረው እንዲሰሩ እንደሚደረግ አመልክተው፤ ፍቃድ ከተሰጣቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀቶች መካከል 148 የሚሆኑት በቡና ዘርፍ የሚሰማሩ መሆናቸውንም አክለዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ያካተቱ የተሽከርካሪ ታርጋዎችን ሥራ ላይ ሊያውል ነው
Jan 13, 2026 81
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሁን እየተጠቀመበት ያለውን የተሽከርካሪ ታርጋ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ባካተተ አዲስ ታርጋ ሊቀይር መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል አስታወቁ። የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወር የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሂዷል።   የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንደተናገሩት ፖሊስ አሁን እየተጠቀመባቸው ያሉ የተሽከርካሪ ታርጋዎችን ሙሉ በሙሉ በመቀየር አዳዲስና ዘመናዊ ታርጋዎችን በቅርቡ ስራ ላይ ለማዋል ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል። ይህም ተቋሙ የወንጀል መከላከልና ምርመራ ስራውን በዘመናዊ መንገድ ለመምራት ከጀመራቸው የሪፎርም ስራዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።   አዲሱ ታርጋ የረቀቁ የቴክኖሎጂ ቁልፎች ያሉት ሲሆን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስን ብቻ የሚወክል፣ የተቋሙን የሙያ ብቃት እንዲሁም የዲሲፕሊን ደረጃ የሚያንፀባርቅ መሆኑን ገልጸዋል። ኮሚሽነር ጀነራሉ አዲሱ ታርጋ ታትሞ በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በይፋ ጥቅም ላይ እንደሚውል አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያን በአቪዬሽን ዘርፍ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችል አቅም እየተገነባ ነው - ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር)
Jan 13, 2026 69
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያን በአቪዬሽን ዘርፍ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችል አቅም እየተገነባ መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ለሁለት ተቋማት የስራ ፈቃድ ሰጥቷል። የስራ ፈቃዱ የተሰጠው በአውሮፕላን ጥገና ዘርፍ በኢትዮጵያ አየር ሃይል ውስጥ ለተቋቋመው እና ለግል አየር መንገዶች ጥገና ለሚሰጠው ተቋም ነው። ባለስልጣኑ በተመሳሳይ ለዓለም አቀፍ የካርጎ አቪዬሽን አገልግሎት ደግሞ የአቪዬሽን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የስራ ፈቃድ ሰጥቷል።   የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያን የበረራ ትራንስፖርት (አቪዬሽን) ማዕከል ለማድረግ የተለያዩ የለውጥ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው፡፡ በዚህም በዘርፉ የኢትዮጵያን ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ አቅም እየተገነባ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ግንባታውን በይፋ ያስጀመሩት የቢሾፍቱ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል፡። በዛሬው ዕለትም ለሁለቱ ተቋማት የተሰጠው የስራ ፈቃድ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን አንስተዋል፡፡ ለኢትዮጵያ አየር ሃይል በጥገና ዘርፍ የተሰጠው የስራ ፈቃድ የግል አየር መንገዶች ለአውሮፕላን ጥገና የሚያወጡትን ወጪ በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በተመሳሳይ የዓለም አቀፍ ካርጎ አቪዬሽን አገልግሎት የአቪዬሽን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ፈቃድ ማግኘቱ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሃይል ለማፍራት በሚደረገው ሀገራዊ ጉዞ ትርጉም ያለው ሚና እንደሚኖረው አስታውቀዋል። ማሰልጠኛው ከኢትዮጵያ አልፎ በአህጉር ደረጃ ባለሙያዎችን ለማፍራት ለሚደረገው እንቅስቃሴ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዮሃንስ አበራ በበኩላቸው፤ ለተቋማቱ እውቅና የተሰጠው አስፈላጊውን መስፈርት ማሟላታቸው ተረጋግጦ መሆኑን ተናግረዋል። በስነ-ስርዓቱ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር)፣ የኢፌዴሪ የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
የተቋሙ የዘመናዊነት ጅማሮና ዲጂታል ኢትዮጵያ ይዞት የመጣው ዕድል
Jan 13, 2026 72
ኢትዮጵያ ዘመናዊነት መላበስ በጀመረችበት ወቅት ለህዝብ አገልግሎት እንዲሰጡ ከተቋቋሙ ቀደምት ተቋማት መካከል አንዱ ነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፡፡ አገልግሎቱ አሰራሩን ሊያቀላጥፉ የሚችሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀምና የደንበኞችን እርካታ መጨመር ባለመቻሉ በተደጋጋሚ ቅሬታ ሲያስተናግድ ቆይቷል። በለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ዘመናዊ፣ ዘመን ተሻጋሪና ጠንካራ የመንግሥት የአገልግሎት ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ሪፎርም መካሄዱ ይታወቃል። የመንግስት አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ በማዘመን ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ከብልሹ አሰራር ለማጽዳት የተጀመረው ጥረት ሕብረተሰቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ እርካታ እንዲኖረው እያደረገ ይገኛል። ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ኤሌክትሪክ ወሳኝ እንደመሆኑ አገልግሎቱ ለዚህ አስቻይ ሁኔታን ሊፈጥሩ የሚችሉ አሰራሮችን መተግበር ግድ ይለዋል። አገልግሎቱ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የኤሌክትሪክ ሽፋንን ለማሳደግ የጀመራቸው ሥራዎች ውጤታማ እየሆኑ ይገኛሉ። ነገር ግን ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት የተያዘው ግብ እውን እንዲሆን ተቋሙን ማዘመን ወሳኝ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አሁን ካለው ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታ አንጻር አሰራርን ከማዘመንና ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ውጪ በቀደመው አሰራር ሀገርን ማሻገር አይቻልም ብለዋል። ይህን ተከትሎ አገልግሎቱ አሰራሩን በቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግ፣ ልምድ ካላቸው ተቋማት ጋር በጋራ መስራት እንዲሁም የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ለቴክኖሎጂ ምቹ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የተያዙ ግቦች እውን እንዲሆኑ ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ነው ያስረዱት። ዋና ሥራ አሥፈጻሚው እንደሚሉት ተቋማቸው ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የደንበኞችን እርካታ የሚጨምሩ አሰራሮችን ተግባራዊ ማድረግ ጀምሯል። ለአብነት የደንበኞችን እንግልት ለመቀነስና ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው የአገልግሎት ክፍያቸውን የሚፈጽሙበት አሰራር ተግባራዊ ማድረጉን ገልጸዋል። አገልግሎቱ ከመልካም አስተዳደርና ከሙስና ጋር ተያይዞ ተደጋጋሚ ቅሬታ ሲነሳበት እንደነበር አስታውሰውም የጥቆማ አቀባበሉን በማዘመን ለቅሬታዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት ተጀምሯል ብለዋል። ተቋሙ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ወስጥ ዘመናዊና የደንበኞችን ፍላጎት የሚያረካ እንዲሆን የጀመራቸውን ሥራዎች የበለጠ እንደሚያጠናክርም አረጋግጠዋል።  
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂክ እቅድ የሀገርን እድገትና ማንሰራራት እውን ለማድረግ ወሳኝ ነው
Jan 13, 2026 53
አሶሳ፤ ጥር 5/2018 (ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂክ እቅድ የሀገርን እድገትና ማንሰራራት እውን ለማድረግ ወሳኝ የልማት ዘርፍ መሆኑን የዘርፉ ምሁር ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ይፋ ሲያደርጉ በሰጡት ማብራሪያ ዲጂታል ኢትዮጵያ ፍትሐዊ እና አስተማማኝ እንዲሁም ትክክለኛ መረጃን ተደራሽ ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን መግለፃቸው ይታወሳል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተገኘውን ስኬት በመሰነቅ በዘርፉ ልማት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችልና የሀገርን እድገትና ማንሰራራት የሚያረጋግጥ መሆኑ ይታመናል። በመሆኑም ስትራቴጂክ እቅዱን ለማሳካት ከመንግሥት ጥረት ባለፈ የግሉ ዘርፍና አጠቃላይ የዜጎች የተቀናጀ ጥረትና ተሳትፎ ወሳኝ ይሆናል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት እና በኢንፎርሜሽን እና ኮሚዩኒኬሽን ኢንጂነሪግ ተባባሪ ፕሮፌሰር መልካሙ ደሬሳ (ዶ/ር)፤ ለዲጂታል ልማት መንግስት የሰጠው ትኩረት የዓለምን ነባራዊ እውነታ በተገነዘበ መልኩ መሆኑን ገልጸዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ ከዓለም ጋር ውድድር የሚገባበት በመሆኑ ለዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ ከመስራት ውጭ አማራጭ የሌለ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም መሰረት ያለፉት አምሰት ዓመታት ትግበራ እና ቀጣይ የተያዘው አቅጣጫ በብዙ መልኩ የኢትዮጵያን ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትግበራ በዘርፉ ልማት ጥሩ መሰረት ያኖረ መሆኑን አንስተው የቀጣዩ ስትራቴጂክ እቅድ ደግሞ የላቀ ውጤት የሚመጣበት ስለመሆኑ አስረድተዋል። በቀጣይ የአርቲፊል ኢንተለጀንስ እና ሌሎች ዘመን አመጣሽ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀምና በመወዳደር ለሀገር ልማትና እድገት መስራት ከሁላችንም ይጠበቃል ሲሉም አስገንዝበዋል። የንግድ ስርዓቱን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግም አስፈላጊ መሆኑን አንስተው የመሶብ አንድ ማእከልን ማስፋት፣ ፋይዳን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ማድረግና የዲጅታል ግብይትን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት የሚወሰነው በሁሉም ጥረትና ትብብር ሲሆን በተለይም የኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢንተርኔት አገልግሎትን ማስፋት ወሳኝ ይሆናል።
ስፖርት
ከማላጋ እስከ አፍሪካ ዋንጫ፤ የሞሮኮው አዲስ እንቁ ብራሂም ዲያዝ
Jan 13, 2026 67
  የግል ክህሎት፣ ፈጣን አስተሳሰቡ እና በጠባብ ክፍተቶች ውስጥ ሰብሮ የመግባት አቅሙ ሙገሳ እንዲጎርፍለት አድርጓል። አንድ ለአንድ ሲገናኝ ተከላካዮችን በፈጣን አካላዊ ቅልጥፍና እና በድንገት አቅጣጫ በመቀየር የሚያልፍበት መንገድ እንዲሁም የመፍጠር አቅሙ የተመልካቾችን ቀልብ የሚይዝ ነው። የአማካይ እና የአጥቂ መስመርን በማገናኘት እና በአስገራሚ ሁኔታ አጭር ኳሶችን በማቀበልም የተዋጣለት ተጫዋች ነው ማለት ይቻላል። በቦታ አያያዙ የእግር ኳስ ልኅቀቱ ከፍተኛ ነው የሚል አድናቆት ከእግር ኳስ ባለሙያዎች አግኝቷል። ኳስን ሲያንከባልልም ለዐይን ይስባል። ከክህሎቱ እና ከማራኪ እንቅስቃሴው ባለፈ ወደ ኋላ እየመለሰ ተከላካዮችን ያግዛል፣ ኳስ ይነጥቃል። ይህ ተጫዋች የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ክስተት የሆነው የሞሮኮው ብራሂም ዲያዝ ነው። የ26 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ዲያዝ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አምስት ጨዋታዎችን አድርጎ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ነው። አዘጋጇ ሞሮኮ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ መክፈቻ ኮሞሮስን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የውድድሩን የመጀመሪያ ግብ አስቆጥሯል።   ብራሂም አብዱልቃድር ዲያዝ የተወለደው እ.አ.አ ኦገስት 3 ቀን 1999 በስፔን ማላጋ ግዛት ነው። እናቱ ስፔናዊ አባቱ ሞሮኳዊ ናቸው። ዲያዝ ያደገው በማላጋ ነው። እግር ኳስንም በአንዳሉሺያዊቷ ከተማ ሲጫወት ቆይቷል። በ16 ዓመቱ ካደገበት ማላጋ በመውጣት እ.አ.አ በ2015 ወደ ማንችስተር ሲቲ ወጣት አካዳሚ በ200 ሺህ ፓውንድ ወጪ ተዘዋወረ። ዲያዝ እ.አ.አ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2016 በካራባኦ ካፕ (በቀድሞ አጠራሩ ሊግ ካፕ) ማንችስተር ሲቲ ከስዋንሲ ሲቲ ባደረገው ጨዋታ በ80ኛው ደቂቃ በኬሌቺ ኢናቺዩ ተቀይሮ በመግባት ለውኃ ሰማያዊዎቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያውን ጨዋታ ካደረገ ከሶስት ቀናት በኋላ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለሶስት ዓመታት የሚያቆየውን ፕሮፌሽናል ኮንትራት ተፈራርሟል። እ.አ.አ ኖቬምበር 21 ቀን 2017 ማንችስተር ሲቲ ከፌይኖርድ ሮተርዳም ጋር ባደረገው የሻምፒዮናስ ሊግ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል። በወቅቱ ብራሂም ስተርሊን መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ሰዓት ላይ ነበር ተቀይሮ የገባው። ዲያዝ በውኃ ሰማያዊዎቹ ማልያ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የተጫወተው እ.አ.አ ዲሴምበር 19 ቀን 2017 ነው። ማንችስተር ሲቲ ከሌስተር ሲቲ በካራባኦ ካፕ ጨዋታ ላይ ለ88 ደቂቃዎች ተሰልፎ ተጫውቷል።   እ.አ.አ ጃንዋሪ 20 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን 3 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በወቅቱ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ያነሳ ሲሆን፤ በውድድር ዓመቱ አራት ጨዋታዎች ላይ ብቻ ተሳትፎ ያደረገው ብራሂም ዲይዝ የሜዳሊያ ሽልማት አግኝቷል። እ.አ.አ ኦገስት 5 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ቼልሲን 2 ለ 0 ባሸነፈበት የኮሙዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ላይ በፊል ፎደን ተቀይሮ በመግባት ለ15 ደቂቃዎች ተጫውቷል። ዲያዝ እ.አ.አ 2018/19 ማብቂያ ላይ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የመጀመሪያ ግቦቹን ለሲቲ አስቆጥሯል። በማንችስተር ሲቲ ያለው ውል እ.አ.አ 2019 ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት ስሙ ከዝውውር ጋር በስፋት ይነሳ ነበር። ዲያዝ እ.አ.አ ጥር 2019 በ17 ሚሊዮን ዩሮ ከማንችስተር ሲቲ ወደ ሪያል ማድሪድ ተዘዋወረ። ለስድስት ዓመታት የሚያቆየውን ውልም ፈርሟል። የክንፍ ተጫዋቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን በነጮቹ ማልያ ያደረገው እ.አ.አ ጥር 9 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ ሌጋኔን በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ 3 ለ 0 ባሸነፈበት ወቅት ነው። ከአራት ቀናት በኋላ በስፔን ላሊጋ ሪያል ማድሪድ ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ ተቀይሮ በመግባት በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያ ግቡን ለማስቆጠር ሶስት ወራትን ጠብቋል። እ.አ.አ ግንቦት 12 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ በላሊጋው በሪያል ሶሲዬዳድ 3 ለ 1 ሲሸነፍ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በወቅቱ ዲያዝ ስድስት ጨዋታዎች ላይ በላሊጋው የተጫወተ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ዓመቱ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ሪያል ማድሪድ እ.አ.አ በ2021/21 የውድድር ዓመት ብራሂም ዲያዝ ወደ ኤሲ ሚላን በውሰት ማምራቱን ይፋ አደረገ። ዲያዝ ሚላን እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2020 ክሮቶኔን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ የመጀመሪያ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ ግንቦት 2021 ኤሲ ሚላን ጁቬንቱስን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ያስቆጠረው ግብም ተጠቃሽ ነው። ዲያዝ በኤሲ ሚላን የውሰት ውሉ ሲያበቃ በድጋሚ ለሁለት ዓመታት በውሰት የሚቆይበት ስምምነት ሪያል ማድሪድ ከጣልያኑ ክለብ ጋር የተፈራረመ ሲሆን፤ ውሉ ሚላን ተጫዋቹን የማቆየት መብት ሰጥቶታል። እ.አ.አ መስከረም 15 ቀን 2021 ኤሲ ሚላን በሻምፒዮንስ ሊጉ የ3 ለ 2 ሽንፈት ሲያስተናግድ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ግቡን አስቆጥሯል። በ2023 ኤሲ ሚላን ቶተንሃም ሆትስፐርስን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ 1 ለ 0 ሲያሽንፍ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023 ሰኔ ወር ላይ ሪያል ማድሪድ ዲያዝ ከኤሲ ሚላን የሶስት ዓመታት የውሰት ቆይታ በኋላ ወደ ክለቡ መመለሱን አሳውቋል። ተጫዋቹ በኤሲ ሚላን ቆይታው 91 ጨዋታዎችን አድርጎ 13 ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ዲያዝ ወደ ሪያል ማድሪድ ከተመለሰ በኋላ ኮንትራቱን እስከ 2027 አራዝሟል። እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2023 ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ሪያል ማድሪድ ላስ ፓልማስን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ አስቆጥሯል።   የክንፍ መስመር ተጫዋቹ ሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥ እና በአውሮፓ መድረክ በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ላይ ግብ በማስቆጠር እና ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ዲያዝ እስከ አሁን ለሪያል ማድሪድ ባደረጋቸው 129 ጨዋታዎች 20 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከነዚህም ውስጥ 13ቱ በላሊጋው ያስቆጠራቸው ናቸው። ከክለብ ወጣ ስንል የተጫዋቹን የብሔራዊ ቡድን ቆይታ እናገኛለን። ዲያዝ በታዳጊነቱ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ለስፔን ወጣት ቡድኖች ተጫውቷል። እ.አ.አ በ2016/17 የውድድር ዘመን ለስፔን ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በ16 ዓመቱ ተሰልፎ መጫወት ችሏል። በተለይም አዘርባጃን እ.አ.አ በ2017 ባዘጋጀችው 15ኛው የአውሮፓ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ላይ ያሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆት አስችሮታል። በዚያ ቀጥለው በነበሩ ዓመታትም ለስፔን ከ19 እና ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቷል። ብራሂም ዲያዝ በስፔን ታዳጊና ወጣት ቡድኖች ላይ በአጠቃላይ 28 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። የስፔን ታዋቂ የስፖርት ጋዜጣ ማርካ እ.አ.አ ጥር 23 ቀን 2023 ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን መጫወት ማቀዱን የሚመለከት ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ከዜግነቱ ጋር በተያያዘ ያሉ አንዳንድ የአስተደዳር ጉዳዮች በወቅቱ መፍትሄ አግኝተዋል። ይሁንና ኮትዲቯር እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሞሮኮው አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከተጫዋቹ ጋር በተደረገ የቅድሚያ ስምምነት ለተጫዋቹ ጥሪ አልተደረገለትም። ዲያዝ እ.አ.አ መጋቢት 10 ቀን 2024 ለሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሀገሪቷ ብሔራዊ መጫወት እንደሚፈልግ በይፋ ማሳወቁን ማርካ በወቅቱ ዘግቧል። ጥያቄውም ተቀባይነት አገኘ። በወቅቱ የሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ብሔራዊ ቡድኑ ከአንጎላ እና ሞሪታኒያ ጋር ለነበረበት የወዳጅነት ጨዋታ ለዲያዝ ጥሪ አድርገውለታል። እ.አ.አ መጋቢት 22 ቀን 2024 ሞሮኮ አንጎላን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። እ.አ.አ ጥቅምት 6 ቀን 2024 ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከጋቦን ጋር ባደረገችው ጨዋታ 4 ለ 1 ስታሸንፍ የመጀመሪያ ግቡን ለሞሮኮ ማስቆጠር ቻለ። እ.አ.አ ሕዳር 15 ቀን 2024 ሞሮኮ በማጣሪያው ጋቦንን 5 ለ 1 ስትረታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። ከሶስት ቀናት በኋላ ሞሮኮ ከሌሴቶ ጋር ባደረገችው የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ 7 ለ 0 ስታሸንፍ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር በሀገሩ ማልያ የመጀመሪያ ሀትሪኩን ሰርቷል። እ.አ.አ ጥቅምት 2025 ሞሮኮ ራባት ላይ ኮንጎ ሪፐብሊክን 1 ለ 0 በማሸነፍ በስፔን ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተይዞ የነበረውን 15 ተከታታይ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ክብረ ወሰን በመስበር ወደ 16 ማድረስ ችላለች። በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ ላይ ዲያዝ ተሰልፎ ተጫውቷል። የሞሮኮ ተከታታይ የማሸነፍ ጉዞ 19 ጨዋታዎች ደርሶ የነበረ ሲሆን በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከማሊ ጋር አንድ አቻ ስትለያይ አብቅቷል።   ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማጣሪያ ብታልፍም አስቀድማ ውድድሩን እንድታዘጋጅ እድል አግኝታ የነበረው ጊኒ በዝግጅት ማነስ ምክንያት በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ከሁለት ዓመት በፊት አዘጋጅነቷ ተነጥቆ ለሞሮኮ ተሰጥቷል። ሞሮኮ የዘንድሮውን ውድድር በደማቅ ሁኔታ እያካሄደች ትገኛለች። በውድድሩ ላይ ጎልተው ከታዩ ተጫዋቾች መካከል ብራሂም ዲያዝ ተጠቃሽ ነው። በአፍሪካ ዋንጫው እስከ አሁን ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። በተሰለፈባቸው በእያንዳዱ ጨዋታዎች ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን በአምስት የአፍሪካ ዋንጫ ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። ሞሮኮ በሩብ ፍጻሜው ማሊን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሯል። ሀገሩ ወደ ግማሽ ፍጻሜ እንድታልፍ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱንም እየመራ ይገኛል። ሞሮኮ በዚሁ ግስጋሴዋ ከቀጠለች ዲያዝ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና ኮከብ ተጫዋች የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። ሞሮኮ በግማሽ ፍጻሜው ከናይጄሪያ ጋር ረቡዕ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ታደርጋለች። ዲያዝ በዚህ ጨዋታ ላይ ልዩነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። አንዳንድ የእግር ኳስ ተንታኞች ብራሂም ዲያዝ እ.አ.አ በ2026 ወጥነት ያለው ብቃት ማሳየት ከቻለ የአፍሪካ ኮከብ ተጫዋችነት ሽልማቱን የሚወስድበት የለም እያሉ ይገኛሉ። ሞሮኳውያን በተጫዋቹ ፍቅር ልባቸው ከንፏል። በየጨዋታው ዲያዝ ዲያዝ እያሉ ከፍተኛ ድጋፍ እና ሙገሳ እየሰጡት ይገኛሉ። እሱም በድንቅ ብቃቱ ምላሽ እየሰጣቸው ነው። በተወለደበት ማላጋ ከተማ የጀመረው የእግር ኳስ ሕይወት በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የበለጠ አብቧል። የሞሮኮው አዲሱ ኮከብ ብራሂም ዲያዝ ቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወት በስኬት እና በድል የደመቀ እንደሚሆን ከአሁኑ ድንቅ ብቃቱ ተነስቶ መናገር ይቻላል።
አካባቢ ጥበቃ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው የአካባቢውን ስነምህዳር በመጠበቅ ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል
Jan 13, 2026 110
አሶሳ፤ ጥር 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሲከናወን የቆየው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የአካባቢውን ስነምህዳር በመጠበቅ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የዘንድሮው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ደረጃ አሶሳ ዞን ቡልድግሉ ወረዳ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ሀሊፋ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የአካባቢውን ስነምህዳር በመጠበቅ ምርታማነት እንዲጨምር አድርጓል። በተለይም የተፋሰስ ልማት ስራ በሚከናወንባቸው አካባቢዎች የሚተከሉ ችግኞች አፈርና ውሃን ከመጠበቅ ባለፈ ለአርሶአደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ እያስገኙ ነው ብለዋል።   በዘንድሮው ዓመት ከ57 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለማከናወን እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ህብረተሰቡ ጥቅሙን በመረዳት በየአካባቢው ተሳትፎውን እያሳደገ መሆኑን ጠቅሰዋል። በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በደለል እንዳይሞላ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም ኃላፊው አንስተዋል።   የቡልድግሉ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በክሪ አብዱላሂ በበኩላቸው፤ በወረዳው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ መከናወን ከጀመረ ወዲህ የደን ሽፋን እያደገ እና የአካባቢው አየር ንብረት እየተስተካከለ መምጣቱን ተናግረዋል። ወረዳው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አቅራቢያ በመገኘቱ የሚከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው አክለዋል። በመርሃግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።  
የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት እና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራ የልማትና የዕድገት ግቦችን ለማሳካት እያገዘ ነው
Jan 13, 2026 85
በደሌ፤ ጥር 5/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል እየተከናወነ የሚገኘው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት እና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራ የልማትና የዕድገት ግቦችን ለማሳካት እያገዘ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። በኦሮሚያ ክልል ለቀጣዮቹ ሁለት ወራት የሚከናወነው የዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ስራ በዛሬው ዕለት በክልል ደረጃ በቡኖ በደሌ ዞን ዳቦ ሐና ወረዳ ተጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ፣ የዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ስራ ከ6 ሺህ 300 በላይ ተፋሰሶች ላይ ይከናወናል ብለዋል።   ባለፉት ዓመታት በክልሉ በተከናወነው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ የክልሉ የደን ሽፋን መጨመሩንና በብዙ ተጎድተው የነበሩ አከባቢዎች በማገገማቸው ምርታማነትም በመጨመር ላይ እንደሚገኝ አንስተዋል። የተፋሰስ ልማት ስራው በተለይም በግብርናው ዘርፍ ተቀርጸው እየተተገበሩ የሚገኙ ኢንሼቲቮች ስኬት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል። በአጠቃላይ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት እና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራ የልማትና የዕድገት ግቦችን ለማሳካት ትልቅ አበርክቶ አለው ብለዋል። ዘንድሮም በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ በጠንካራ የህዝብ ተሳትፎ ታጅቦ የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል። የቡኖ በደሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማን ደኑ በበኩላቸው በዞኑ የተጀመረው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በ222 ተፋሰሶች ላይ የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል።   በዞኑ በአየር ንብረት ለውጥ እና በአፈር አሲዳማነት ምክንያት የሚደርሰውን የምርታማነት መቀነስን ለመከላከል በተፋሰስ ልማቱ የሚከናወኑ ስራዎች እንደሚጠናከሩ ተናግረዋል። በበጋው ወራት የተፋሰስ ልማት የሚከናወንበት መሬት በክረምቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተለያዩ ቸግኞች ለመሸፈን የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል። ለዚህም ከ200 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በዞኑ እየተዘጋጁ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተፋሰስ ልማት ስራው የተሳተፉ አርሶ አደሮችም ስራው በአፈርና እና ውሃ ሀብቶች ላይ የሚደርሱ ችግሮችን በመከላከል ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ዘንድሮም ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።  
በመዲናዋ እየተከናወነ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራ አካታች እና ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን የያዘ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jan 12, 2026 124
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራ አካታች እና ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን የያዘ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። በአዲስ አበባ በሚገኙ ስምንት ወንዞች ላይ 47 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የወንዝ ዳርች ልማት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። ከንቲባዋ ይህን ያሉት በከተማዋ እየተገነቡ ከሚገኙ ስምንት የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች መካከል የቀበና እና የግንፍሌ ወንዞችን የሥራ ሂደት በገመገሙበት ወቅት ነው።   ከንቲባ አዳነች አቤቤ ወንዞች ለከተማ መቆርቆር፣ ለከተማ ውበት እና ለከተማ ልማት ዋና እና መሰረት ናቸው ሲሉም ገልጸዋል። ይሁንና በአዲስ አበባ ወንዞች የብክለት ችግር የሚፈጠርባቸው፣ የተለያዩ ወንጀለኞች የሚደበቁበት፣ የበሽታ መንስኤዎች በመሆን ብዙ ተጽእኖዎችና ችግሮች ሲያደርሱ መቆየታቸውን አመልክተዋል። በኢትዮጵያ ወንዞች ላይ በተደረገ ጥናት በመዲናዋ ብቻ 76 ወንዞች እንዳሉ ጠቁመው ወንዞቹ ከየመጸዳጃ ቤቱ ፍሳሽ የሚገባባቸው ሆነው መገኘታቸውን ነው የገለጹት። በለውጡ ዘመን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወንዞቻችንን እናጽዳ ሸገርን እናስውብ በሚል አዲስ አበባን እንደ ስሟ አበባ ከማድረግ ራዕይ ጋር በማስተሳሰር በ2012 ዓ.ም የወንዞች ዳርቻ ልማት መጀመሩን አስታውሰዋል።   ስራው አዲስ አበባ ውብ አበባ መሆን የምትችለው ወንዞች ከጸዱ እና ወደ ተፈጥሯዊ ማንነታቸው ከተመለሱ እና ከዳኑ ብቻ እንደሆነ በትልቅ መረዳት የተጀመረ እንደሆነም ነው ያስረዱት። የወንዝ ዳርቻ ልማት በወቅቱ ለኢትዮጵያ አዲስ በመሆኑ የውጭ የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ አስፈልጎ እንደነበር አመልክተዋል። ፕሮጀክቱ በተጀመረ አምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚሆን ብቻ ልማት መከናወኑን ጠቅሰው በራሳችን ሀገር በቀል አቅም ለምን አንሰራም? በሚል የዛሬ ዓመት በአዲስ መልክ ስራው መጀመሩን ጠቁመዋል። በኢትዮጵያውያን አቅም በስምንት ወንዞች ላይ የ47 ኪሎ ሜትር የውንዝ ዳርቻ ልማት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም አብራርተዋል። ከዚህ ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚይዘው ከእንጠጦ እስከ ፒኮክ ያለው መሆኑን ገልጸው የውስጥ ለውስጥ መንገዶች እና መሰረተ ልማቶችን ሳይጨምር 21 ኪሎ ሜትር እንደሚረዝም ገልጸዋል። ከእንጠጦ እስከ ፒኮክ ባለው የወንዝ ዳርቻ ውስጥ ሰባት ፓርኮች እንደሚገኙና ንግድን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶችን እንደሚሰጡም ተናግረዋል። በአጠቃላይ የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራው አካታች እና ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን የያዘ መሆኑን አክለዋል።
የውሃ ሃብት ሁሉንም የህይወት ዘርፍ የሚነካ ወሳኝ አህጉራዊ የህልውና ጉዳይ ነው
Jan 12, 2026 133
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018(ኢዜአ)፦ የውሃ ሃብት ለአፍሪካውያን ሁሉንም የህይወት ዘርፍ የሚነካ ወሳኝ አህጉራዊ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤና 48ኛው የሥራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ከየካቲት 4 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል። የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤን አጀንዳ፣ የውሳኔ ሀሳብና ሪፖርት ለማዘጋጀት የሚደረገው 51ኛው የሕብረቱ አባል ሀገራት ቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ ዛሬ ተጀምሯል።   የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ትኩረቱን በውሀ ላይ ያደረገ ነው። የውሃ ሃብት ለአፍሪካውያን ሁሉንም የህይወት ዘርፍ የሚነካ ወሳኝ አህጉራዊ የህልውና ጉዳይ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፤ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤና ኮፕ 30ን ለመከታተል ትክክለኛ ምርጫ ነው ብለዋል። የኮፕ 32 በአፍሪካ ኢትዮጵያ እንድታስተናግድ በመመረጧ ኩራት ይሰማናል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ለጉባኤው ዝግጅት በጋራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰላምና ጸጥታ ዙሪያ ብዙም ለውጥ ባልታየበት ሁኔታ እንደሚካሄድ ገልጸው፤ በሱዳን፣ ሊቢያ፣ በሳህል ቀጣና እና በምስራቃዊ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ያለው ችግር እስካሁን አልተፈታም ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የሰላምና ደህንነት ምክር ቤት የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን መፍትሔ እንዲያገኙ ለማስቻል በሰላምና ደህንነት የሪፎርም በጋራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ላይ የሚጣሉ የታሪፍ ገደቦች፣ የሚሰበሰበው ሀብት መቀነስና የጉዞ ክልከላዎች የዓለም ህግና ሥርዓቱን በመሸርሸር አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደሩ መሆኑንም አንስተዋል። በመሆኑም ይህንን ኢ-ፍትሐዊነት ለመከላከል በሕብረቱ አባል ሀገራት መካከል ትብብርና አንድነትን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።   በአፍሪካ ሕብረት የአንጎላ ቋሚ ተወካይ እና 51ኛው የሕብረቱ አባል ሀገራት ቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ሚጉኤል ቤምቤ በአፍሪካ ዘላቂ የውሃ ሀብት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ መሪ ሀሳብ ውኃን መሰረት ያደረገ መሆኑን በማንሳት፤ በአፍሪካ በውኃ ጉዳዮች ላይ የሚነሱ ግጭቶችን መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ይመክራል ብለዋል፡፡ የዚህን መሪ ሀሳብ አመንጪ ኢትዮጵያ መሆኗን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ሚጉኤል፤ ለአፍሪካውያን የቀረበ ሀሳብ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ ቀጣናዊ ትብብርና ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለመፍጠር የኢንዱስትሪ አብዮት ወሳኝ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በሁሉም አባል ሀገራት ገቢራዊ መደረግ አለበት ነው ያሉት፡፡ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አካል ነው ያሉት ፕሮፌሰር ሚጉኤል፤ አህጉራዊ ግቦችን ለማሳካት ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡  
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ውኃ ለአፍሪካ የኅልውና ጉዳይ ነው - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Jan 12, 2026 132
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ ውኃ ሁሉንም ዘርፍ የሚነካ አህጉራዊ የኅልውና ጉዳይ መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የሕብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ስብሰባው"ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሐሳብ የሚደረግ ነው።   በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ፣ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት ትኩረቱን ያደረገው በውኃ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ውኃ በሁሉም አይነት እጅጉን ወሳኝ የሆነ ሀብት እና የኅልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ አህጉራዊ ግቦቹን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አስገንዝበዋል። በብራዚል ቤለም የተካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) ትኩረት ከተሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል አንዱ መሆኑንም አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በምታዘጋጀው 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ውኃ አንዱ አጀንዳ እንደሚሆንም ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማዘጋጀት በመመረጧ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ያሉ ሲሆን፤ ለጉባኤው ስኬታማነት ሕብረቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ሰላም እና ደኅንነት የአፍሪካ አንገብጋቢ አጀንዳ መሆኑን የገለጹት ሊቀ መንበሩ ሱዳን፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሊቢያን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ኢ-ሕገመንግሥታዊ ለውጦች አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው፤ ሀገራት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንዲያከብሩ አሳስበዋል። የአፍሪካ ሕብረት ተቋማዊ ሪፎርም እና ኢኮኖሚያዊ ትሥሥርን ጨምሮ ለአህጉራዊ አጀንዳዎች እየሠራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። አህጉራችን ፈተናዎች ቢኖሩባትም በጋራ ከቆምን እናልፋቸዋለን ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የዛሬው ስብስባ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን፤ የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ መሆኑ ይታወቃል።
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ይጀመራል
Jan 12, 2026 180
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚደረግ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣የሕብረቱ አባል አገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብስባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል አገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
የቻይና አፍሪካ ትብብር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል
Jan 8, 2026 163
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማሕሙድ አሊ ዩሱፍ ከቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ጋር ውይይት አካሄዱ። ውይይቱ እያደገ የመጣው የቻይና አፍሪካ ትብብርን ማጠናከር ላይ ያለመ ነው ተብሏል። ቻይና የአፍሪካ እውነተኛ አጋር መሆኗን የገለፁት የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ያተኮረው ፖሊሲ ጠንካራ ወዳጅነት እንዲፈጠር ማድረጉን ገልፀዋል። የቻይና አፍሪካ ግንኙነት በተለያዩ የትብብር ማዕቀፎች እያደገ መምጣቱንም ተናግረዋል። ከውይይቱ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ሁለቱ ወገኖች የዓለም ደቡባዊ ቀጣና (Global South) ሀገራትን መብትና ጥቅም ለማስከበር፣ የሉዓላዊነትን ክብር ለመጠበቅ እና ዓለም አቀፍ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በጋራ ለመሥራት መስማታቸውን አስታውቀዋል። በውይይቱ ወቅት የቻይናን የአምስት ዓመት የልማት ዕቅድ ከአፍሪካ ኅብረት የ2063 አጀንዳ ሁለተኛው የዐሥር ዓመት ትግበራ ጋር በማጣጣም ዘመናዊነትን ለማምጣት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ምክክር መደረጉ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነቶችን ጨምሮ፣ ቻይና ያቀረበቻቸውን ዓለም አቀፍ የደኅንነትና የልማት ተነሳሽነቶች በጋራ ለመደገፍ ከስምምነት መድረሳቸውን ኢቢሲ ዘግቧል። በተጨማሪም የተፈረሙ የትብብር ስምምነቶችን በተግባር በመተርጎም እና የንግድ ልውውጥን በማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት በጋራ መግለጫቸው አረጋግጠዋል።
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ በቀጣዩ ሳምንት ይጀመራል
Jan 8, 2026 158
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ(PRC) መደበኛ ስብሰባው ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ያተኮረ ነው። በስብሰባው የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብሰባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብሰባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 513
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 468
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 687
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 842
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል።   ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ።   ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡   የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።  
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 479
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 428
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 1082
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3419
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3044
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1933
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7749
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6229
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 59657
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53711
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34354
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31892
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27291
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26165
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25706
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25583
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 59657
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53711
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34354
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31892
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ከማላጋ እስከ አፍሪካ ዋንጫ፤ የሞሮኮው አዲስ እንቁ ብራሂም ዲያዝ
Jan 13, 2026 67
  የግል ክህሎት፣ ፈጣን አስተሳሰቡ እና በጠባብ ክፍተቶች ውስጥ ሰብሮ የመግባት አቅሙ ሙገሳ እንዲጎርፍለት አድርጓል። አንድ ለአንድ ሲገናኝ ተከላካዮችን በፈጣን አካላዊ ቅልጥፍና እና በድንገት አቅጣጫ በመቀየር የሚያልፍበት መንገድ እንዲሁም የመፍጠር አቅሙ የተመልካቾችን ቀልብ የሚይዝ ነው። የአማካይ እና የአጥቂ መስመርን በማገናኘት እና በአስገራሚ ሁኔታ አጭር ኳሶችን በማቀበልም የተዋጣለት ተጫዋች ነው ማለት ይቻላል። በቦታ አያያዙ የእግር ኳስ ልኅቀቱ ከፍተኛ ነው የሚል አድናቆት ከእግር ኳስ ባለሙያዎች አግኝቷል። ኳስን ሲያንከባልልም ለዐይን ይስባል። ከክህሎቱ እና ከማራኪ እንቅስቃሴው ባለፈ ወደ ኋላ እየመለሰ ተከላካዮችን ያግዛል፣ ኳስ ይነጥቃል። ይህ ተጫዋች የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ክስተት የሆነው የሞሮኮው ብራሂም ዲያዝ ነው። የ26 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ዲያዝ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አምስት ጨዋታዎችን አድርጎ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ነው። አዘጋጇ ሞሮኮ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ መክፈቻ ኮሞሮስን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የውድድሩን የመጀመሪያ ግብ አስቆጥሯል።   ብራሂም አብዱልቃድር ዲያዝ የተወለደው እ.አ.አ ኦገስት 3 ቀን 1999 በስፔን ማላጋ ግዛት ነው። እናቱ ስፔናዊ አባቱ ሞሮኳዊ ናቸው። ዲያዝ ያደገው በማላጋ ነው። እግር ኳስንም በአንዳሉሺያዊቷ ከተማ ሲጫወት ቆይቷል። በ16 ዓመቱ ካደገበት ማላጋ በመውጣት እ.አ.አ በ2015 ወደ ማንችስተር ሲቲ ወጣት አካዳሚ በ200 ሺህ ፓውንድ ወጪ ተዘዋወረ። ዲያዝ እ.አ.አ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2016 በካራባኦ ካፕ (በቀድሞ አጠራሩ ሊግ ካፕ) ማንችስተር ሲቲ ከስዋንሲ ሲቲ ባደረገው ጨዋታ በ80ኛው ደቂቃ በኬሌቺ ኢናቺዩ ተቀይሮ በመግባት ለውኃ ሰማያዊዎቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያውን ጨዋታ ካደረገ ከሶስት ቀናት በኋላ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለሶስት ዓመታት የሚያቆየውን ፕሮፌሽናል ኮንትራት ተፈራርሟል። እ.አ.አ ኖቬምበር 21 ቀን 2017 ማንችስተር ሲቲ ከፌይኖርድ ሮተርዳም ጋር ባደረገው የሻምፒዮናስ ሊግ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል። በወቅቱ ብራሂም ስተርሊን መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ሰዓት ላይ ነበር ተቀይሮ የገባው። ዲያዝ በውኃ ሰማያዊዎቹ ማልያ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የተጫወተው እ.አ.አ ዲሴምበር 19 ቀን 2017 ነው። ማንችስተር ሲቲ ከሌስተር ሲቲ በካራባኦ ካፕ ጨዋታ ላይ ለ88 ደቂቃዎች ተሰልፎ ተጫውቷል።   እ.አ.አ ጃንዋሪ 20 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን 3 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በወቅቱ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ያነሳ ሲሆን፤ በውድድር ዓመቱ አራት ጨዋታዎች ላይ ብቻ ተሳትፎ ያደረገው ብራሂም ዲይዝ የሜዳሊያ ሽልማት አግኝቷል። እ.አ.አ ኦገስት 5 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ቼልሲን 2 ለ 0 ባሸነፈበት የኮሙዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ላይ በፊል ፎደን ተቀይሮ በመግባት ለ15 ደቂቃዎች ተጫውቷል። ዲያዝ እ.አ.አ 2018/19 ማብቂያ ላይ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የመጀመሪያ ግቦቹን ለሲቲ አስቆጥሯል። በማንችስተር ሲቲ ያለው ውል እ.አ.አ 2019 ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት ስሙ ከዝውውር ጋር በስፋት ይነሳ ነበር። ዲያዝ እ.አ.አ ጥር 2019 በ17 ሚሊዮን ዩሮ ከማንችስተር ሲቲ ወደ ሪያል ማድሪድ ተዘዋወረ። ለስድስት ዓመታት የሚያቆየውን ውልም ፈርሟል። የክንፍ ተጫዋቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን በነጮቹ ማልያ ያደረገው እ.አ.አ ጥር 9 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ ሌጋኔን በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ 3 ለ 0 ባሸነፈበት ወቅት ነው። ከአራት ቀናት በኋላ በስፔን ላሊጋ ሪያል ማድሪድ ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ ተቀይሮ በመግባት በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያ ግቡን ለማስቆጠር ሶስት ወራትን ጠብቋል። እ.አ.አ ግንቦት 12 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ በላሊጋው በሪያል ሶሲዬዳድ 3 ለ 1 ሲሸነፍ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በወቅቱ ዲያዝ ስድስት ጨዋታዎች ላይ በላሊጋው የተጫወተ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ዓመቱ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ሪያል ማድሪድ እ.አ.አ በ2021/21 የውድድር ዓመት ብራሂም ዲያዝ ወደ ኤሲ ሚላን በውሰት ማምራቱን ይፋ አደረገ። ዲያዝ ሚላን እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2020 ክሮቶኔን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ የመጀመሪያ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ ግንቦት 2021 ኤሲ ሚላን ጁቬንቱስን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ያስቆጠረው ግብም ተጠቃሽ ነው። ዲያዝ በኤሲ ሚላን የውሰት ውሉ ሲያበቃ በድጋሚ ለሁለት ዓመታት በውሰት የሚቆይበት ስምምነት ሪያል ማድሪድ ከጣልያኑ ክለብ ጋር የተፈራረመ ሲሆን፤ ውሉ ሚላን ተጫዋቹን የማቆየት መብት ሰጥቶታል። እ.አ.አ መስከረም 15 ቀን 2021 ኤሲ ሚላን በሻምፒዮንስ ሊጉ የ3 ለ 2 ሽንፈት ሲያስተናግድ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ግቡን አስቆጥሯል። በ2023 ኤሲ ሚላን ቶተንሃም ሆትስፐርስን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ 1 ለ 0 ሲያሽንፍ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023 ሰኔ ወር ላይ ሪያል ማድሪድ ዲያዝ ከኤሲ ሚላን የሶስት ዓመታት የውሰት ቆይታ በኋላ ወደ ክለቡ መመለሱን አሳውቋል። ተጫዋቹ በኤሲ ሚላን ቆይታው 91 ጨዋታዎችን አድርጎ 13 ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ዲያዝ ወደ ሪያል ማድሪድ ከተመለሰ በኋላ ኮንትራቱን እስከ 2027 አራዝሟል። እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2023 ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ሪያል ማድሪድ ላስ ፓልማስን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ አስቆጥሯል።   የክንፍ መስመር ተጫዋቹ ሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥ እና በአውሮፓ መድረክ በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ላይ ግብ በማስቆጠር እና ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ዲያዝ እስከ አሁን ለሪያል ማድሪድ ባደረጋቸው 129 ጨዋታዎች 20 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከነዚህም ውስጥ 13ቱ በላሊጋው ያስቆጠራቸው ናቸው። ከክለብ ወጣ ስንል የተጫዋቹን የብሔራዊ ቡድን ቆይታ እናገኛለን። ዲያዝ በታዳጊነቱ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ለስፔን ወጣት ቡድኖች ተጫውቷል። እ.አ.አ በ2016/17 የውድድር ዘመን ለስፔን ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በ16 ዓመቱ ተሰልፎ መጫወት ችሏል። በተለይም አዘርባጃን እ.አ.አ በ2017 ባዘጋጀችው 15ኛው የአውሮፓ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ላይ ያሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆት አስችሮታል። በዚያ ቀጥለው በነበሩ ዓመታትም ለስፔን ከ19 እና ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቷል። ብራሂም ዲያዝ በስፔን ታዳጊና ወጣት ቡድኖች ላይ በአጠቃላይ 28 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። የስፔን ታዋቂ የስፖርት ጋዜጣ ማርካ እ.አ.አ ጥር 23 ቀን 2023 ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን መጫወት ማቀዱን የሚመለከት ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ከዜግነቱ ጋር በተያያዘ ያሉ አንዳንድ የአስተደዳር ጉዳዮች በወቅቱ መፍትሄ አግኝተዋል። ይሁንና ኮትዲቯር እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሞሮኮው አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከተጫዋቹ ጋር በተደረገ የቅድሚያ ስምምነት ለተጫዋቹ ጥሪ አልተደረገለትም። ዲያዝ እ.አ.አ መጋቢት 10 ቀን 2024 ለሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሀገሪቷ ብሔራዊ መጫወት እንደሚፈልግ በይፋ ማሳወቁን ማርካ በወቅቱ ዘግቧል። ጥያቄውም ተቀባይነት አገኘ። በወቅቱ የሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ብሔራዊ ቡድኑ ከአንጎላ እና ሞሪታኒያ ጋር ለነበረበት የወዳጅነት ጨዋታ ለዲያዝ ጥሪ አድርገውለታል። እ.አ.አ መጋቢት 22 ቀን 2024 ሞሮኮ አንጎላን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። እ.አ.አ ጥቅምት 6 ቀን 2024 ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከጋቦን ጋር ባደረገችው ጨዋታ 4 ለ 1 ስታሸንፍ የመጀመሪያ ግቡን ለሞሮኮ ማስቆጠር ቻለ። እ.አ.አ ሕዳር 15 ቀን 2024 ሞሮኮ በማጣሪያው ጋቦንን 5 ለ 1 ስትረታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። ከሶስት ቀናት በኋላ ሞሮኮ ከሌሴቶ ጋር ባደረገችው የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ 7 ለ 0 ስታሸንፍ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር በሀገሩ ማልያ የመጀመሪያ ሀትሪኩን ሰርቷል። እ.አ.አ ጥቅምት 2025 ሞሮኮ ራባት ላይ ኮንጎ ሪፐብሊክን 1 ለ 0 በማሸነፍ በስፔን ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተይዞ የነበረውን 15 ተከታታይ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ክብረ ወሰን በመስበር ወደ 16 ማድረስ ችላለች። በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ ላይ ዲያዝ ተሰልፎ ተጫውቷል። የሞሮኮ ተከታታይ የማሸነፍ ጉዞ 19 ጨዋታዎች ደርሶ የነበረ ሲሆን በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከማሊ ጋር አንድ አቻ ስትለያይ አብቅቷል።   ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማጣሪያ ብታልፍም አስቀድማ ውድድሩን እንድታዘጋጅ እድል አግኝታ የነበረው ጊኒ በዝግጅት ማነስ ምክንያት በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ከሁለት ዓመት በፊት አዘጋጅነቷ ተነጥቆ ለሞሮኮ ተሰጥቷል። ሞሮኮ የዘንድሮውን ውድድር በደማቅ ሁኔታ እያካሄደች ትገኛለች። በውድድሩ ላይ ጎልተው ከታዩ ተጫዋቾች መካከል ብራሂም ዲያዝ ተጠቃሽ ነው። በአፍሪካ ዋንጫው እስከ አሁን ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። በተሰለፈባቸው በእያንዳዱ ጨዋታዎች ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን በአምስት የአፍሪካ ዋንጫ ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። ሞሮኮ በሩብ ፍጻሜው ማሊን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሯል። ሀገሩ ወደ ግማሽ ፍጻሜ እንድታልፍ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱንም እየመራ ይገኛል። ሞሮኮ በዚሁ ግስጋሴዋ ከቀጠለች ዲያዝ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና ኮከብ ተጫዋች የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። ሞሮኮ በግማሽ ፍጻሜው ከናይጄሪያ ጋር ረቡዕ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ታደርጋለች። ዲያዝ በዚህ ጨዋታ ላይ ልዩነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። አንዳንድ የእግር ኳስ ተንታኞች ብራሂም ዲያዝ እ.አ.አ በ2026 ወጥነት ያለው ብቃት ማሳየት ከቻለ የአፍሪካ ኮከብ ተጫዋችነት ሽልማቱን የሚወስድበት የለም እያሉ ይገኛሉ። ሞሮኳውያን በተጫዋቹ ፍቅር ልባቸው ከንፏል። በየጨዋታው ዲያዝ ዲያዝ እያሉ ከፍተኛ ድጋፍ እና ሙገሳ እየሰጡት ይገኛሉ። እሱም በድንቅ ብቃቱ ምላሽ እየሰጣቸው ነው። በተወለደበት ማላጋ ከተማ የጀመረው የእግር ኳስ ሕይወት በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የበለጠ አብቧል። የሞሮኮው አዲሱ ኮከብ ብራሂም ዲያዝ ቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወት በስኬት እና በድል የደመቀ እንደሚሆን ከአሁኑ ድንቅ ብቃቱ ተነስቶ መናገር ይቻላል።
አማድ ዲያሎ - የአፍሪካ እግር ኳስ  ብሩህ ተስፋ
Jan 9, 2026 261
ተጫዋቹ አዲሱ ሳሙኤል ኤቶ የሚል ስያሜ እየተሰጠው ይገኛል። ፍጥነቱን ከዲዲየር ድሮግባ ጋር ያነጻጽሩታል። ለተጋጣሚ ተጫዋቾች የራስ ምታት እና ፈተና የሆነውን ግራ እግሩን ከሌላኛው የግራ እግር ምትሃተኛ ሪያድ ማህሬዝ ጋር የሚያወዳድሩም አልጠፉም።   በዚህ አካሄዱ ከቀጠለ ያለ ምንም ጥርጥር ወደፊት በእግር ኳስ ከምንመለከታቸው ኮከቦች አንዱ ሊሆን ይችላል እየተባለለት ይገኛል። ይህ ተጫዋች በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ዓመታት ታሪክ ሀትሪክ የሰራ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ተጫዋች ነው። እያወራን የምንገኘው የማንችስተር ዩናይትድ 16 ቁጥር ማልያ ለባሽ አማድ ዲያሎ ነው። የ23 ዓመቱ ኮትዲቯራዊ ተስፈኛ ተጫዋች በቀያዮቹ ሴጣኖች እያሳየ ያለው ብቃት ከብዙዎች ዘንድ ሙገሳ አስችሮታል፣ አድናቆት እንዲጎርፍለት አድርጓል። ወደ ኋላ መለስ እንበልና የአማድ ዲያሎን መነሻ እንመልከት። ካሜሮን ከአዘጋጇ ሞሮኮ ለግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው አማድ የተወለደው እ.አ.አ ጁላይ 11 2002 በኮትዲቭዋር መዲና አቢጃን ነው። ተጫዋቹ በአፍሪካ ምድር ቢወለድም ገና በህጻንነት እድሜው ነበር ወደ ጣልያን የተሰደደው። የእግር ኳስ ህይወቱን የጀመረው እ.አ.አ በ2014 በጣልያን ሬጂዮ ኢሚሊያ ግዛት በሚገኘው ቦካ ባርኮ የታዳጊ ቡድን ነው። ቡድኑን በተቀላቀለበት ዓመት የገና በዓል (ክሪስማስን) በማስመልከት በተካሄደ ውድድር ላይ በ12 ዓመቱ ኮከብ ግብ አግቢ ሲሆን ያሳየው አስደማሚ ብቃት የብዙዎችን ቀልብ ሳበ። ይህ የገና በዓል ውድድር አማድን እ.አ.አ በ2015 በቦካ ባርኮ ቡድን እንዲመዘገብ አደረገው። ተጫዋቹ በቡድኑ ብዙም አልቆየም። የበርካታ የጣልያን ሴሪአ ክለቦች አይን አረፈበት። ብዙም ሳይቆይ በዛው በ2015 ወደ ጣልያኑ አትላንታ አመራ።   አማድ ከእ.አ.አ 2015 እስከ 2019 ለአትላንታ ታዳጊ ቡድን የተጫወተ ሲሆን እ.አ.አ 2019 እና 20 ለዋናው ቡድን ተጫውቷል። ለዋናው ቡድን አራት ጨዋታዎችን አድርጎ ማስቆጠር የቻለው አንድ ግብ ብቻ ነው። የእንግሊዙ ክለብ ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹ በጣልያኑ ክለብ ባሳየው ብቃት በ18 ዓመት እድሜው እ.አ.አ ጃንዋሪ ወር 2021 በአምስት ዓመት ኮንትራት በ37 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዩሮ አስፈርሞታል። ተጫዋቹ ወደ ማንችተር ሲመጣ ቀጥታ ወደ ዋናው ቡድኑ አልተቀላቀለም። በቡድኑ ከ23 ዓመት በታች ጨዋታውን ማድረግ ጀመረ። አማድ የመጀመሪያ ጨዋታውን ለማንችስተር ያደረገው እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 18 2021 ቡድኑ ከሪያል ሶሲዬዳድ ጋር ባደረገው የዩሮፓ ሊግ ጨዋታ ነው። በዛው ዓመት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እና አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ላይ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ዲያሎ ከእ.አ.አ 2022-2023 ባለው ጊዜ ሬንጀርስ እና ሰንደርላንድ በውሰት የተጫወተ ሲሆን በቡድኖቹ ባደረጋቸው 47 ጨዋታዎች 16 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል።   እ.አ.አ በ2023/24 አማድ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ በመመለስ በድጋሚ መጫወት ጀምሯል። በክለቡም ድንቅ ብቃቱን እያሳየ መምጣት ጀመረ። እ.አ.አ ጥር 17 2025 ማንችስተር ዩናይትድ ከሊጉ ከወረደው ሳውዝሃምፐን ጋር በነበረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር በ12 ደቂቃ ውስጥ ሶስት ግቦችን አስቆጥሮ ሀትሪክ በመስራት ቡድኑ 3 ለ 1 አንዲያሸንፍ ያደረገበት መንገድ አድናቆት አስችሮታል። በዚህም አማድ በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ታሪክ የመጀመሪያ ሀትሪክ የሰራ አፍሪካ ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። አማድ በቀያዮቹ ሴጣኖች ማልያ እስከ አሁን ባደረጋቸው 53 ጨዋታዎች 11 ግቦችን አስቆጥሯል። ተጫዋቹ ከክለቡ በተጨማሪ ለኮትዲቯር ብሄራዊ ቡድን በመጫወት ላይ ይገኛል። እ.አ.አ 2021 ኮትዲቯር ከኒጀር ጋር ባደረገችው ጨዋታ በ86ኛው ደቂቃ ተቀይሮ በመግባት ለብሄራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ለሀገሩ እስከ አሁን ባደረጋቸው 15 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። የመጀመሪያ ጎሉን ኮትዲቯር በ2021 በወዳጅነት ጨዋታ ቡርኪናፋሶን 2 ለ 1 ስታሸነፍ ነበር ያስቆጠረው። አማድ ዲያሎ ዘንድሮ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ድንቅ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል። አማድ በውድድሩ ላይ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች ሶስት ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን አንድ ለግብ የሚሆን ግብ አመቻችቶ አቀብሏል። ኮትዲቯር ከሞዛምቢክ፣ ካሜሮን እና ቡርኪናፋሶ ጋር ባደረገቻቸው ጨዋታዎች የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተምርጧል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቯር ሩብ ፍጻሜ እንድትደርስ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። ኮትዲቯር ከግብጽ በሩብ ፍጻሜው ነገ ከግብጽ ጋር ምሽት አራት ሰዓት ላይ በአጋዲር ስታዲየም የምታደርገው ጨዋታ በጉጉጉት ይጠበቃል። ሀገሩ በጠዋታው ላይ ከአማድ ብዙ ትጠብቃለች። ወደ ክለብ እንቅስቃሴው ስንመለስ አማድ በማንችስተር ዩናይትድ ስብስብ ውስጥ ቁልፍ የሚባል ተጫዋች ነው። ፈጣን ኳስን የማንከበላል ክህሎቱ፣ ፍጥነቱ ፣ የቴክኒክ አቅሙ፣ ጨዋታን የማንበብ ብቃቱ እና ሁለቱንም እግሩን የመጠቀም አቅሙ አልፎም ተጫዋቾችን በቄንጥ የሚያልፍበት መንገድ ተጫዋቹን እያስወደሰው ነው። አማድ ዲያሎ ከክንፍ ተጫዋችነቱ ባሻገር የአጥቂ አማካይ ሆኖ መጫወትም ይችላል። እ.አ.አ በ2020 የ18 ዓመት ልደቱን ተከትሎ ተጫዋቹ ስሙን ከአማድ ትራኦሬ ወደ አማድ ዲያሎ አስቀይሯል። አማድ ካለው ድንቅ ብቃት አንጻር ወደፊት በክለብ እና ብሄራዊ ቡድን ደረጃ ድንቅ ጊዜን ካሳለፉ ታዋቂ የአፍሪካ ተጫዋቾች ተርታ የመሰለፉ ጉዳይ አያጠራጥርም።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም