ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
አርባምንጭ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ተጋሩ 
Apr 13, 2026 170
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት አርባምንጭ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ፍፁም ጥላሁን በ29ኛው እና ተገኑ ተሾመ በ36ኛው ደቂቃ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ቅዱስ ጊዮርጊስ መሪ ሆኗል። ናይጄሪያዊው ጄሮም ፍሊፕ በ42ኛው እና ሴኔጋላዊው ማማዱ ሴክ በ97ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፏቸው ግቦች ለአርባምንጭ ከተማ ወሳኝ አንድ ነጥብ አስገኝተዋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ የ2 ለ 0 ውጤቱን ማስመዝገብ አልቻለም።   ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ32 ነጥብ ደረጃውን ከ15ኛ ወደ 12ኛ ከፍ አድርጓል። ቡድኑ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ማስመዝገብ አልቻለም።   አርባምንጭ ከተማ በ23 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል። በሀዋሳ ከተማ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሜዳ ውሃ በመያዙ፣ በሀዋሳ ከተማ እና በምድረ ገነት ሽሬ መካከል ሊደረግ የነበረው የምሽት 12 ሰዓት ጨዋታ በዳኞች ውሳኔ ሳይካሄድ ቀርቷል። የሊጉ አክሲዮን ማህበር የመርሐ ግብሩን አዲስ የጨዋታ ቀን እና ቦታ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ገልጿል። ዛሬ በተደረጉ የ27ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች መቀሌ 70 እንደርታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 ሲረታ ሸገር ከተማ እና ነገሌ አርሲ አንድ አቻ ተለያይተዋል።
በሐረሪ ክልል 250 አባወራዎችን ያካተተ ሞዴል መንደር ሊገነባ ነው
Apr 13, 2026 125
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል በገጠር ኮሪደር ልማት በቀጣይ ሁለት ወራት 250 አባዎራዎችንና እማወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሞዴል መንደር እንደሚገነባ የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ አስታወቁ። በክልሉ የገጠር ኮሪደር ዐቢይ ኮሚቴ ዕቅድ እና አፈጻጸም ላይ ውይይት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ርዕሰ መሥተዳድሩ እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት የተጀመረው የኮሪደር ልማት ከፅዱና ውብ አካባቢ ባለፈ ለዜጎች ምቹ የመኖሪያ ሥፍራ እንዲፈጠር እያስቻለ ነው።   በዚህም መሠረት በሐረር ከተማ በኮሪደር ልማት ዘርፍ የተመዘገበውን ውጤት በገጠሩ ክፍል ለማስፋት እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል። በገጠር አካባቢ የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎችም፤ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ሁኔታ ለመቀየር የሚያስችሉ መሆናቸውን ነው ያመላከቱት። ለአብነትም አርሶ አደሩ ያለውን ሀብትና ፀጋ በአግባቡ ተጠቅሞ ኢኮኖሚውን በማሳደግ በዚያው ልክ የተመቸ ኑሮ እንዲመራ የሚያግዝ መሆኑን ነው ያስረዱት። በክልሉ የሞዴል ገጠር መንደር መፈጠሩን የገለጹት ርዕሰ መሥተዳድሩ፤ ሞዴል መንደሩም ውኃና የኃይል አቅርቦትን ጨምሮ ሌሎች መሠረተ-ልማቶች እንዲሟሉ ተደርጓል ብለዋል። በቀጣይ ሁለት ወራትም 250 አባዎራዎችንና እማወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሞዴል የአርሶ አደሮች የመኖሪያ መንደር ለመገንባት ይሠራል ነው ያሉት። የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራ በላቀ ቁርጠኝነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠው፤ ለዚህም አርሶ አደሩ እያከናወነው የሚገኘውን የላቀ ተሳትፎና ድጋፍ እንዲያጠናክር አሳስበዋል። በየደረጃው የሚገኘው አመራርም ሥራዎችን በቅንጅት እና በትብብር እንዲሠራ ነው ያሳሰቡት። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የገጠር_ኮሪደር
በወራጅ ቀጠና የሚገኘው መቀሌ 70 እንደርታ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አገኘ
Apr 13, 2026 137
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር መቀሌ 70 እንደርታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፍፁም አለሙ እና ኮትዲቯራዊው አብዱላጢፍ ባምባ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ግብ አስቆጣሪው ኮትዲቯራዊው አብዱላጢፍ ባምባ በ82ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ወጥቷል። ዳዊት ገብሩ ለወልዋሎ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው መቀሌ 70 እንደርታ በ26 ነጥብ 19ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ላለመውረድ በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በሊጉ ያስመዘገባቸውን ድሎች ብዛትም ወደ አምስት ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በሊጉ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ29 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ወልዋሎ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም።
በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪዎች ለተኪና ወጪ ንግድ ምርቶች እድገት ትኩረት ተሰጥቶ ተከናውኗል
Apr 13, 2026 138
ባህርዳር፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአምራች ኢንዱስትሪዎች ለተኪና ወጪ ንግድ የሚውሉ ምርቶችን በዓይነትና በብዛት የማምረት ስራ ትኩረት ተሰጥቶት መከናወኑን የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ። መንግስት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ተግባራዊ በማድረግ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ያለውን ችግር በጋራ በመፍታት ዘላቂነት ያለው እድገትና ተወዳዳሪነት እንዲመዘገብ እያደረገ ይገኛል። በዚህም በርካታ ኢንዱስትሪዎች የመሰረተ ልማትና ሌሎች ችግሮቻቸው እየተፈታ የማምረት አቅማቸው እየጎለበተ ውጤታማ በመሆን ላይ ናቸው።   ኢንዱስትሪዎች ወጪ ምርቶችን እንዲሁም ተኪ ምርቶችን በራስ አቅም በማምረት የውጭ ምንዛሬ እጥረትን በማቃለል ለሀገር እድገት ያላቸው አስተዋጽኦ እየጨመረ የመጣበት ሁኔታ እየተፈጠረ ይገኛል ። ‎ከዚሁ ጋር ተያይዞ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅንቄ በመታገዝ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም እንዲጎለብት ተደርጓል። በወራቶቹ በንቅናቄው በተደረገ ጥረት 137 ከፍተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የውሃ፣ የመብራትና የመንገድ መሰረተ ልማቶች ተሟልተውላቸው ወደ ማምረት ሥራ ተሸጋግረዋል።   በአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና የኤክስፖርት ምርቶችን በዓይነትና በብዛት በማምረት ለሀገር እድገት ጥቅም ላይ ለማዋል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ‎በዚህም ከ554 ሺህ ቶን በላይ ተኪ ምርት በማምረት መንግስት ሊያወጣ የነበረውን 650 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል ብለዋል። ‎እንዲሁም በአምራች ኢንዱስትሪዎች የተመረተ 123 ሺህ ቶን ምርት ለውጭ ገበያ መቅረቡን ጠቅሰዋል። ‎በተጨማሪም ከ306 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ከ2ሺህ 925 በላይ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች ፈቃድ ወስደው ወደ ተግባር እንዲገቡ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። ‎ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ማምረት ሲሸጋገሩ ከ450 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩም አመላክተዋል። ‎በተቋሙ ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመተግበር የአገልግሎት አሰጣጡን ግልጽ፣ ፍትሃዊ፣ ምቹና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ‎በቀጣይም ቢሮው አምራች ኢንዱስትሪዎችን በልዩ ሁኔታ በመደገፍ ፈጥነው ወደ ማምረት ሥራ እንዲሸጋገሩና ወደምርት የገቡትም ምርታቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።
የሚታይ
በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ለተሰማሩ ባለሀብቶች የገቢ ግብር ዕፎይታ ተፈቀደ
Apr 13, 2026 274
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ ግብዓትና ምርት ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሀብቶች ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑ በገንዘብ ሚኒስቴር ውሳኔ ተላለፈ። ሚኒስቴሩ ይህንን የፈቀደው የንግድ ቀጠናዎቹ ባለሀብቶችን ይበልጥ የሚስቡ እንዲሆኑ ለማድረግ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት በሚፈለገው መጠን እንዳያድግ ምክንያት ከሆኑት መካከል የካፒታል እጥረት፣ የግብዓት አቅርቦት ችግር እና የባለሙያ እጥረት በዋነኛነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ በመረጃው ጠቁሟል። በመሆኑም እነዚህን ችግሮች ደረጃ በደረጃ በማቃለል የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ልማትን ማሳደግ እንደሚገባ አስታውቋል። በዚህም መሠረት ግብዓቶች እና ሌሎችም ምርቶች በበቂ መጠን ለገበያ እንዲቀርቡ ለማድረግ፣ አስመጪዎች ምርቱን ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት የሚከፍሉት ቀረጥ እና ታክስ ውስን በሆነው ካፒታላቸው ላይ የሚያሳድረውን ጫና ማቃለል አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በነዚህ ምክንያቶች አስመጪዎች ግብዓቶችን እና ምርቶችን ቀረጥና ታክስ ሳይከፍሉ ወደ አገር አስገብተው፣ ለግብዓቱ ወይም ለምርቱ ገበያ ባገኙ ጊዜ ቀረጥና ታክሱን የሚከፍሉበትን አሰራር የሚፈቅድ የነፃ የንግድ ቀጣና አሰራር ተዘርግቷል። ይህንን ሥርዓት የሚያስፈጸሙ ነፃ የንግድ ቀጣናዎችም በየአካባቢው የተቋቋሙ መሆኑ ተመልክቷል። ይህንን ተከትሎም በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ ተሰማርተው ምርትና ግብዓት ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሀብቶች ከላይ ከተጠቀሰው የታክስ አከፋፈል ስርዓት በተጨማሪ ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑ ተደርጓል። በመሆኑም ባለሀብቶች ይህንን ዕድል በመጠቀም በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ እንዲሰማሩ የገንዘብ ሚኒስቴር ጥሪውን አስተላልፏል።
ኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማብሰር የሚያስችሉ ተጨባጭ ተግባራትን እያከናወነች ነው
Apr 13, 2026 414
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም በመሸፈን የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማብሰር የሚያስችሉ ተጨባጭ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ እልፍ ጸጋዎች፣ እምቅ አቅሞች፣ ብሩህ ተስፋዎች፣ ተዝቀው የማያልቁ እሴቶችና ባለታሪክ ህዝቦች ያሏት ሀገር ናት፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ አቅሞቿና አንጡራ ሀብቶቿ ዜጎቿን ከድህነት ኢትዮጵያን ከተረጂ ሀገራት መደብ ሳያወጧት ዓመታት ነጉደዋል፡፡ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በስንዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ አሻራና በሌሎችም ሀገራዊ ጉዳዮች የተጀመሩ ኢኒሼቲቮች ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን እያመጡ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳብ አመንጪነት የሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም እሳቤ እየተተገበረ ነው፡፡ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ምንም ያልጎደላት ምንም ያላነሳት ሆና እያለ ለምን ተረጂ፣ ለማኝ ትሆናለች ከሚል ዕሳቤ የመነጨ ኢኒሼቲቭ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢኒሼቲቩ ተረጅነትና ጠባቂነት ወዴት እየወሰደን ነው ከሚል ቁጭት በመነሳት መጀመሩን ገልጸው፤ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ከመቻል ባለፈ የክብር የነጻነትና የሀገር ሉዓላዊነት ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ መንግሥት ተረጂነትን ለማስቀረትና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በግብርናው መስክ ተጨባጭ ለውጦችን ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም በመሸፈን የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማብሰር የሚያስችል የሚጨበጥ ተግባር እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የአደጋ ምላሽ ፈንድ በማቋቋም፣ የሎጂስቲክ ስርዓቱን በማሳለጥና ከውጭ የሚገባውን ስንዴ በማስቀረት ክልሎች የመጠባበቂያ ክምችታቸውን እያሳደጉ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ ለረጅም ዘመን እሴት ሆኖ የቀጠለውን የቤተሰብ ኃላፊነትና የማህበረሰብ አጋርነት ተቋማዊ ይዘት እንዲኖረው እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ 10 ክልሎች ሰብዓዊ ድጋፍን በራሳቸው አቅም መሸፈን መቻላቸውን የገለጹት ኮሚሽነሩ፥ አሁን ላይ ከውጭ የምናስገባው ስንዴ የለም ብለዋል። ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የጀመረችው ጉዞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አመራር ሰጪነት በከፍተኛ ተነሳሽነት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፤ በስኬታማ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
ሀገርን የማልማት ሥራ በበዓልና በእረፍት ቀናት ሳይገታ ተጠናክሮ ይቀጥላል 
Apr 12, 2026 1182
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 4/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገርን የማልማት ሥራ በበዓልና በእረፍት ቀናት ሳይገታ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ እየተገነባ በሚገኘው የኢንዱስትሪ ክላስተር የሥራ ቦታ በመገኘት በግንባታው ላይ ለሚሳተፉ ሠራተኞች ማዕድ አጋርተዋል።   ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ጊዜ፤ በተለወጠ የሥራ ባሕል በርካታ መሠረተ ልማቶች በጥራት እየተገነቡ መሆኑን ተናግረዋል። እየሰራን ሀገርን እየገነባን በዓልን እናከብራለን ያሉት ከንቲባዋ መስራት የሚያስከብር ተግባር መሆኑንና ከድህነት ለመውጣት በበዓል፣ በእረፍትም ሆነ በሌሊት ጠንክሮ መስራት የግድ እንደሚል አስገንዝበዋል። ይህ የኢንዱስትሪ ክላስተር ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት ለ13 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። ግንባታውን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ሠራተኞች የበዓል ቀናትን ጨምሮ በከፍተኛ ተነሳሽነት እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል።   በዓል ምሉዕ የሚሆነው ከለውጥና ከብልፅግና ጋር ሲያያዝ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ የማዕከሉ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በአሁኑ ወቅት በመጠናቀቅ ላይ እንዳለ ገልጸዋል። ግንባታው ተጠናቆ ማዕከሉ ሥራ ሲጀምር ለበርካታ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ለውጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል። ሠራተኞቹ በበዓላትም ሆነ በእረፍት ቀናት ሳይወሰኑ ሀገርን ለማልማት እያሳዩ ላለው ትጋት ምስጋና አቅርበዋል። በግንባታው ላይ እየተሳተፉ ያሉት ሠራተኞች በሰጡት አስተያየት የተደረገላቸው የማዕድ ማጋራት የሥራ ተነሳሽነታቸውን እንደሚጨምረውና ለሀገር ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል። እንዲህ ያሉ የቅርብ ክትትልና ድጋፎች ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብና ጥራት እንዲጠናቀቅ ትልቅ አቅም እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትንሣኤን በዓል ምክንያት በማድረግ 27ኛውን የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ሥራ አስጀመሩ   
Apr 12, 2026 880
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 4/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ 27ኛውን የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል በጉለሌ ክፍለ ከተማ በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፤ በአዲስ አበባ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስቻሉ ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን ገልጸዋል።   ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችንም በጥራትና በፍጥነት በመገንባት በማህበራዊ ችግር ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም የመዲናዋ የምገባ ማዕከላት እጅ አጠር ዜጎች ማህበራዊ ድጋፍ የሚያገኙበትን ወሳኝ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ጠቀሜታ እያበረከቱ እንደሚገኝ አንስተዋል።   27ኛው የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል በጉለሌ ሶስተኛው ቅርንጫፍ መሆኑን ገልጸው፤ማዕከሉ በርካታ አቅመ ደካማ ወገኖች በቀን አንድ ጊዜ የምግብ አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል እንደሚፈጥር ጠቅሰዋል። በአዲስ አበባ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ግንባታ ስኬት ከፍተኛ ድጋፍ እያደረጉ ለሚገኙ ባለሃብቶችና በጎ አድራጊዎችም ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም የዜጎች የመረዳዳትና መደጋገፍ እሴት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ፀዳለች ሚካኤል በበኩላቸው ፤ በምገባ ማዕከላት የሚከናወነው የምገባ መርሐ ግብር በበዓላት ወቅት ብቻ ሳይሆን በቋሚነት የሚከናወን በመሆኑ ለብዙዎች የሕይወት ተስፋ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል።   አስተያየታቸውን የሰጡ የማዕከሉ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው፤ ከከንቲባዋ ጋር በዓልን በማሳለፋቸው መደሰታቸውን ገልፀው ማዕከሉ አረጋውያንና ሕፃናት የእለት ጉርሳቸውን አጥተው እንዳይቸገሩ ትልቅ እፎይታ የሚፈጥርላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ወጣቶችን በልማት ተጠቃሚ የሚያደርግ የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
Apr 13, 2026 814
ሰመራ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ ወጣቶችን በልማት ተጠቃሚ የሚያደርግ የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ የሰመራ ሎጊያ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም መራዘሙ ይታወሳል። በዚሁ መሰረት በአፋር ክልል የሰመራ ሎጊያ ከተማ ወጣቶችም በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ሀገራዊ ልማትን ለማስቀጠል እና የወጣቶችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የፖለቲካ አማራጭ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ካርዳቸውን እየወሰዱ መሆኑን ነው የተናገሩት። ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ የወሰዱ የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶች ለኢዜአ እንደተናገሩት የምርጫ ካርድ መውሰድ አማራጭ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ መሰረታዊ ጉዳይ ነው።   ወጣት ሃጂ አብዱልለጢፍ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን የፖሊሲ አማራጮች በሚዲያ በሚያደርጉት ክርክሮች በንቃት እየተከታተልኩ ነው ብሏል። ይህም በተለይም የወጣቶችን ጉዳይ ትኩረት አድርጎ የሚንቀሳቀሰውን ፓርቲ ለመምረጥ እንደሚያስችለው ጠቅሶ በምርጫው በንቃት ለመሳተፍም ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሯል ብሏል። ሌላኛው የከተማው ወጣት አብዱ መሐመድ በምርጫው ለመሳተፍ የሚያስችለውን ካርድ መውሰዱን ተናግሯል።   በካርዱም ይበጀኛል የሚለውንና የወጣቶችን ሁለንተናዊ ጥያቄዎች ለመመለስ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ መዘጋጀቱን ጠቁሟል ። የመራጮች ካርድ መውሰዱ ለዴሞክራሲያዊ ግንባታ የበኩሉን ለማበርከትና የዜግነት ግዴታውን ለመወጣት መሰረት በመሆኑ ይህንኑ ተግባራዊ ማድረጉንም አክሏል። የመራጭነት ካርድ መውሰዴ ይጠቅመኛል የምለውን ፓርቲ እንድመርጥ ያስችለኛል ያለው ደግሞ ወጣት የሱፍ መሐመድ ነው።   በዚህም በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ሀገራችን የጀመረችውን የልማት ጉዞ ከግብ ለማድረስና የወጣቶችን ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጥ አማራጭ ፖሊሲ ያለውን ፓርቲን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ሲል ተናግሯል።
የሐረር ከተማ ነዋሪዎች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ድምጻቸውን ለመስጠት ከወዲሁ ተዘጋጅተዋል
Apr 13, 2026 555
ሐረር ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ድምጻቸውን ለመስጠት ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን የሐረር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ነው። በዚህም በሐረሪ ክልል የሚገኙ ነዋሪዎች በምርጫው ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ላይ ናቸው። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ፍሬህይወት አባይነህ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት ከዚህ ቀደም በነበሩት አራት ሀገራዊ ምርጫዎች ላይ በመሳተፍ ይሆነኛል፣ ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ መምረጣቸውን አስታውሰዋል።   በመጪው ግንቦት በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፤ ለዚህም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን እና ድምጻቸውንም ለሀገር ልማትና እድገት ይሰራል ብለው ለሚያምኑት ፓርቲ እንደሚሰጡ ተናግረዋል። የከተማው ነዋሪ አቶ ሀብታሙ ሲፋ በበኩላቸው፤ የዜግነትና ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ እንደወሰዱ ተናግረዋል።   በሚዲያ አማራጮች የሚተላለፈውን የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር በአግባቡ በመከታተል ላይ እንደሚገኙ የተናገሩት አቶ ሀብታሙ፤ ይሆነኛል ለሚሉት ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚገባም ተናግረዋል።   በምርጫው የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ የምንፈልገውን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችል ካርድ ወስደናል ያሉት ደግሞ አጀባ አደም ናቸው። የሚበጀንን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ያሉት አጀባ፤ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ እንዲሆን የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል።
የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ ለማገዝና በምክክር ችግሮችን ለመፍታት የበኩላችንን እንወጣለን- የድሬዳዋ ነዋሪዎች
Apr 10, 2026 2727
ድሬዳዋ፤ ሚያዚያ 2/2018 (ኢዜአ) ፡-የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ ለማገዝና በምክክር ችግሮችን ለመፍታት የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የድሬዳዋ ነዋሪዎች ተናገሩ። በለውጡ ዓመታት በድሬዳዋ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች የተመዘገቡባቸው መሆኑን በብዙ መልኩ ማረጋገጥ ይቻላል። በለውጡ የመጡ ስኬቶችን እውቅና ለመስጠትም የድሬዳዋ ህዝብ ወደ አደባባይ በመውጣት በድጋፍ ሰልፍ እውቅና መስጠት ችሏል። የኢትዮጵያን ተስፋ እና የወደፊት እጣ ፋንታ የሚወስኑ ወሳኝ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው ከዳር እንዲደርሱ የሁላችንም ትብብር፣ ድጋፍና እገዛ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም በለውጡ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ ለማገዝና በምክክር ችግሮችን ለመፍታት የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የድሬዳዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የአፍረን ቀሎ አባገዳ አብዱረዛቅ አህመድ እና የሶማሌ ኢሳ ማህበረሰብ ባህላዊ መሪ ኡጋዝ ተወካይ ሐጂ አብዶ ኡመር፤ በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮች ያስከተሏቸው ስብራቶች እንዳሉ አንስተው በምክክር በዘላቂነት መፍታት ወሳኝ ስለመሆኑ ተናግረዋል። ለዚህም ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ትልቅ ተስፋ የሰነቀ መሆኑን አንስተው ውጤታማ ሊሆን የሚችለው በችግሮቻችን ላይ መክረን ለመፍትሄው በጋራ መስራት ስንችል ነው ብለዋል።   ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አክሊለ ታጠቅ እና አቶ አብዶ ሙሜ፤ በለውጡ የመጡ ስኬቶችን ዘላቂ ለማድረግ ህብረ ብሄራዊ ሀገራዊ አንድነትን ማጽናት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በሀገር ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር የሚቻለው በችግሮቻችን ላይ መክረን የጋራ መፍትሄ መሻት ስንችል ነው ብለዋል።   ለዚህም ዜጎች ያለምንም ልዩነት ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ለትውልድ ግንባታ አደራ ተቀብለን መስራት ስንችል ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዘመናት እየተንከባለሉ የመጡ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር በመፍታት ለትውልዱ የምትመች ሀገር መገንባት ይቻላል በሚል መርህ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።    
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚኖራቸውን የክትትልና ድጋፍ ሚና አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Apr 9, 2026 3596
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፡-የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚኖራቸውን የክትትልና ድጋፍ ሚና አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሳበ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሟል።   በዚሁ ጊዜ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ እጸገነት መንግስቱ፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛል ብለዋል። ባለሥልጣኑም የሲቪል ማህበረሰብ የድርጅቶች ምዝገባና ቁጥጥር፣ ለሀገር ልማትና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚያበረክቱትን አስተዋፅኦ ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሕዊና ዴሞክራሲያዊነትም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላትም፤ ባለስልጣኑ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምዝገባና ክትትል የዲጂታላይዜሽን ሥርዓት ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራትን ጠይቀዋል። በተጨማሪም በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫና በሀገር የልማትና ዴሞክራሲ ባህል ግንባታ የበጎ ፈቃድ ሥራዎች ጋር የተያያዙ አስተያየትና ጥያቄዎችን አቅርበዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ፤ ሀገራዊ ለውጡ የፈጠረው ተቋማዊ የለውጥ እርምጃ ለሰቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንቅስቃሴ አስቻይ ሁኔታን ፈጥሯል ብለዋል። የባለስልጣኑ አገልግሎቶችን ሙሉ ለሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግ መታቀዱን አመልክተው፤ የተወሰኑ አገልግሎቶችን ወደ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የበጎ አድራጎት ስራዎችን ለማሳደግ ‘ቅን ልብ’ የተሰኘ መተግበሪያ ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚደረገውን ክትትል ለማጠናከር ውጤታማና ስጋትን መሰረት ያደረገ የመሰክ ምልከታ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ ከክልሎች ሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ምክር ቤቶች ጋር በጋራ እየተሰራ ነው ብለዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድርጅቶቹን ሚና ለማጎልበት እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችንም አብራርተዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ በበኩላቸው፤ ከምዝገባ ጀምሮ ወደ ስራ የተሰማሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚደረገው ክትትል ለማጠናከር የተሰሩ ስራዎቸን አብራርተዋል። የምክር ቤቱ የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እጸገነት መንግስቱ፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫው ሂደት ገለልተኛና ነጻ ሆነው በስፋት እንዲሰሩ የሚደረገው ክትትል ማጠናከር ያሰፈልጋል ብለዋል። ባለስልጣኑ በዲጂታላይዜሽንና በሰው ሀይል አቅም ግንባታ፣ የበጎ ፍቃደኝነት ስራዎችን ለማጎልበትና የምዝገባና ሂደቱን በጥንቃቄ ለማካሄድ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን አንስተዋል። ድርጅቶቹ በተቋቋሙበት ዓላማ መሰረት እየሰሩ መሆናቸውን እንዲሁም ጠንካራ አገሪቷን የሚመጥኑ ድርጅቶችን ለማስፋፋት መስራት ይገባል ብለዋል።  
ኢትዮጵያ እና ቡሩንዲ የተፈራረሟቸው የመግባቢያ ስምምነቶች ለቀጣናዊ ዘላቂ ልማት ያለውን የሀገራቱን የጋራ ቁርጠኝነት በይፋ የሚያረጋግጡ ናቸው
Apr 9, 2026 2407
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቡሩንዲ የተፈራረሟቸው የመግባቢያ ስምምነቶች ለቀጣናዊ ዘላቂ ልማት ያለውን የሀገራቱን የጋራ ቁርጠኝነት በይፋ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የቡሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንድያይሺሚዬ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተለያዩ የመግባቢያ ስምምነቶች ልውውጥ ላይ ታድመዋል። በመከላከያ፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በውሃና ኢነርጂ፣ በግብርና ፣ በንግድ ፣ በዲጂታል መታወቂያ እና በቱሪዝም ዘርፎች የተፈረሙት እነዚህ ሁሉን አቀፍ ስምምነቶች ለቀጣናዊ ዘላቂ ልማት ያለውን የጋራ ቁርጠኝነት በይፋ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። እነዚህ የመግባቢያ ስምምነቶች የሁለቱን ሀገራት ሰፊ አቅም በመደመር ወደ ብልጽግና ለምናደርገው የጋራ ጉዞ መሠረት የሚጥሉ እንደሆኑም ገልጿል።
የኢትዮጵያን ታሪካዊ ጠላቶች ፍላጎት ለማሳካት የታለመውን የጥፋት መንገድ በመተው የሰላም አማራጭ ተቀብለናል - ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን የቀድሞ አመራር አባላት
Apr 9, 2026 2365
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፡- ቀደም ሲል ሲከተሉት የቆዩት የጥፋት መንገድ አገርንና ሕዝብን የሚጎዳና የታሪካዊ ጠላቶችን ፍላጎት ለማሳካት ያለመ በመሆኑ የሰላም አማራጭ መቀበላቸውን ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን የቀድሞ አመራር አባላት ገለጹ። በጥፋት ቡድኑ ተታለው ጫካ የገቡ ወንድሞቻቸውም ወደ ሠላም አማራጭ እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል። እጃቸውን በሠላም ለመንግስት የሰጡ የጽንፈኛ ቡድኑ የቀድሞ አመራር አባላት ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ እስከአሁን ሲከተሉት የቆዩት መንገድ ለክልሉ ህዝብ አንዳች ጥቅም እንደሌለው በመረዳታቸው የሰላም አማራጭን ተቀብለዋል። በጫካ ቆይታቸው የተረዱት እውነታ "ለሕዝብ እንታገላለን" በሚል መፈክር ሽፋን የቀድሞ ሕወሃትና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ፍላጎት ለማሳካት የተጠለፈ ትግል መሆኑንና ሕዝብን ለጥፋት ለመዳረግ ያለመ አካሄድ መሆኑን ተገንዝበዋል። እጃቸውን በሰላም ከሰጡት ራሱን አፋብን ብሎ ከሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች መካከል የቀድሞ የኮር ፖሊት መምሪያ ኃላፊ ጌራወርቅ ዳኛው፤ የአማራ ሕዝብ ዘላቂ ተጠቃሚነት የሚረጋገጠው በሰላማዊ መንገድ መታገል ብቻ በመሆኑ ሰላማዊ አማራጭን ለመከተል ወስኛለሁ ብሏል። የጽንፈኛ ቡድኑ አመራሮች ከክልሉም ሆነ ከኢትዮጵያ ሕዝብ የልማት ፍላጎት በተጻራሪ በመቆም ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር ተባብረው ጥፋት በማድረስ ላይ ናቸው ያለው ጌራወርቅ፤ በማህበራዊ እሴቶችና መሰረተ ልማቶች ላይ በተደጋጋሚ የሚፈጸመው ጥቃት ከጀርባው የጥፋት ሴራ እንዳለው አመላካች መሆኑን ተናግሯል። ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን የቀድሞ አመራር አባል ሀምሳ አለቃ ፍቅሩ ሙልዬ በበኩሉ፤ የጽንፈኛው ቡድን አመራሮች ከሕዝብ ፍላጎት ይልቅ ለኢትዮጵያ ጠላቶችና ለግል ጥቅማቸው እየሰሩ መሆኑን ጠቁሟል። ለጽንፈኛው ቡድን የተለያዩ ጥያቄዎች ሲነሱ የትግል አጋርን በመፈረጅ የማሸማቀቅና አልፎም ሰበብ ፈልጎ የማስወገድ ተግባር እንደሚፈጸም አስረድቷል። እነርሱ ልጆቻቸውን ውጭ ልከው እያስተማሩ የደሃ ልጆችን ግን ለመስዋዕትነት እየዳረጉ ነው ሲል ሀምሳ አለቃ ፍቅሩ አብራርቷል። ሌላው የቡድኑ የቀድሞ አመራር አባል እና ኮር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር አየነው አስፋው እንደገለጸው፤ ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች ፍላጎት ትግሉን በማራዘም የራሳቸውን ሀብት ማካበት ላይ ማተኮር ነው። ለትግል በሚል የተጀመረው ዓላማ የሕዝብን የልማትና የእድገት ፍላጎት የሚያደናቅፍ፣ አንዳች ፋይዳ የሌለው መሆኑን መረዳቱን አመልክቶ፤ ለህዝብ ጥቅም እንቆማለን የሚሉት የጥፋት ቡድኑ አመራር አባላት ቤት በመስራት፣ ተሽከርካሪ በመግዛትና ሀብት በማካበት መጠመዳቸውን ገልጿል። በጥፋት በድኑ ራሱን የሸዋ ፋኖ ጠቅላይ ግዛት ብሎ የሚጠራው የቀድሞ ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ማንነገረው መለሰ እንደገለጸው፤ የግለሰቦችን የሥልጣን ፍላጎት ለማርካት የሚደረገው እንቅስቃሴ ሀገርን ከመጉዳት የዘለለ ፋይዳ የለውም። የቡድኑ አመራሮች ምንም ዓይነት ግልጽ ፖለቲካዊ እውቀት፣ መርህና ዝግጁነት የሌላቸው መሆኑን ጠቅሶ፤ ሕዝቡ የቡድኑን እውነተኛ ማንነት ሊገነዘብ እንደሚገባም አሳስቧል። ይህ አካሄድ ሕዝብም የማይደግፈው ውጤት የማያመጣ መሆኑን መረዳቱን ጠቅሶ፤ ሰላማዊ አማራጨ በመቀበል ለመጓዝ መምረጡን ተናግሯል። የመረጡት የሰላም አማራጭ የጥፋት ተልዕኮ ሳራዘም በክልሉ ሰላም ግንባታ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት እንደሆነ አስገንዝበዋል። በዚህም እኛ የሰላም አብሪ ሆነናል ያሉት የቀድሞው ጽንፈኛ ቡድን አመራር አባላት፤ በቀጣይም ቀሪ በጫካ የሚገኙ ወንድሞቻችን የመንግስትን የሰላም አማራጭ በመቀበል ለአማራ ህዝብና ለኢትዮጵያ ሰላም መስራት እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።
ፖለቲካ
ወጣቶችን በልማት ተጠቃሚ የሚያደርግ የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
Apr 13, 2026 814
ሰመራ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ ወጣቶችን በልማት ተጠቃሚ የሚያደርግ የፖሊሲ አማራጭ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ የሰመራ ሎጊያ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም መራዘሙ ይታወሳል። በዚሁ መሰረት በአፋር ክልል የሰመራ ሎጊያ ከተማ ወጣቶችም በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ሀገራዊ ልማትን ለማስቀጠል እና የወጣቶችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የፖለቲካ አማራጭ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ካርዳቸውን እየወሰዱ መሆኑን ነው የተናገሩት። ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ የወሰዱ የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶች ለኢዜአ እንደተናገሩት የምርጫ ካርድ መውሰድ አማራጭ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ መሰረታዊ ጉዳይ ነው።   ወጣት ሃጂ አብዱልለጢፍ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን የፖሊሲ አማራጮች በሚዲያ በሚያደርጉት ክርክሮች በንቃት እየተከታተልኩ ነው ብሏል። ይህም በተለይም የወጣቶችን ጉዳይ ትኩረት አድርጎ የሚንቀሳቀሰውን ፓርቲ ለመምረጥ እንደሚያስችለው ጠቅሶ በምርጫው በንቃት ለመሳተፍም ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሯል ብሏል። ሌላኛው የከተማው ወጣት አብዱ መሐመድ በምርጫው ለመሳተፍ የሚያስችለውን ካርድ መውሰዱን ተናግሯል።   በካርዱም ይበጀኛል የሚለውንና የወጣቶችን ሁለንተናዊ ጥያቄዎች ለመመለስ የሚሰራን ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ መዘጋጀቱን ጠቁሟል ። የመራጮች ካርድ መውሰዱ ለዴሞክራሲያዊ ግንባታ የበኩሉን ለማበርከትና የዜግነት ግዴታውን ለመወጣት መሰረት በመሆኑ ይህንኑ ተግባራዊ ማድረጉንም አክሏል። የመራጭነት ካርድ መውሰዴ ይጠቅመኛል የምለውን ፓርቲ እንድመርጥ ያስችለኛል ያለው ደግሞ ወጣት የሱፍ መሐመድ ነው።   በዚህም በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ሀገራችን የጀመረችውን የልማት ጉዞ ከግብ ለማድረስና የወጣቶችን ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጥ አማራጭ ፖሊሲ ያለውን ፓርቲን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ሲል ተናግሯል።
የሐረር ከተማ ነዋሪዎች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ድምጻቸውን ለመስጠት ከወዲሁ ተዘጋጅተዋል
Apr 13, 2026 555
ሐረር ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ድምጻቸውን ለመስጠት ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን የሐረር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ነው። በዚህም በሐረሪ ክልል የሚገኙ ነዋሪዎች በምርጫው ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ላይ ናቸው። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ፍሬህይወት አባይነህ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት ከዚህ ቀደም በነበሩት አራት ሀገራዊ ምርጫዎች ላይ በመሳተፍ ይሆነኛል፣ ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ መምረጣቸውን አስታውሰዋል።   በመጪው ግንቦት በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፤ ለዚህም የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን እና ድምጻቸውንም ለሀገር ልማትና እድገት ይሰራል ብለው ለሚያምኑት ፓርቲ እንደሚሰጡ ተናግረዋል። የከተማው ነዋሪ አቶ ሀብታሙ ሲፋ በበኩላቸው፤ የዜግነትና ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ እንደወሰዱ ተናግረዋል።   በሚዲያ አማራጮች የሚተላለፈውን የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር በአግባቡ በመከታተል ላይ እንደሚገኙ የተናገሩት አቶ ሀብታሙ፤ ይሆነኛል ለሚሉት ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚገባም ተናግረዋል።   በምርጫው የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ የምንፈልገውን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችል ካርድ ወስደናል ያሉት ደግሞ አጀባ አደም ናቸው። የሚበጀንን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ያሉት አጀባ፤ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ እንዲሆን የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል።
የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ ለማገዝና በምክክር ችግሮችን ለመፍታት የበኩላችንን እንወጣለን- የድሬዳዋ ነዋሪዎች
Apr 10, 2026 2727
ድሬዳዋ፤ ሚያዚያ 2/2018 (ኢዜአ) ፡-የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ ለማገዝና በምክክር ችግሮችን ለመፍታት የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የድሬዳዋ ነዋሪዎች ተናገሩ። በለውጡ ዓመታት በድሬዳዋ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች የተመዘገቡባቸው መሆኑን በብዙ መልኩ ማረጋገጥ ይቻላል። በለውጡ የመጡ ስኬቶችን እውቅና ለመስጠትም የድሬዳዋ ህዝብ ወደ አደባባይ በመውጣት በድጋፍ ሰልፍ እውቅና መስጠት ችሏል። የኢትዮጵያን ተስፋ እና የወደፊት እጣ ፋንታ የሚወስኑ ወሳኝ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው ከዳር እንዲደርሱ የሁላችንም ትብብር፣ ድጋፍና እገዛ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም በለውጡ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለስኬት እንዲበቁ ለማገዝና በምክክር ችግሮችን ለመፍታት የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የድሬዳዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የአፍረን ቀሎ አባገዳ አብዱረዛቅ አህመድ እና የሶማሌ ኢሳ ማህበረሰብ ባህላዊ መሪ ኡጋዝ ተወካይ ሐጂ አብዶ ኡመር፤ በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮች ያስከተሏቸው ስብራቶች እንዳሉ አንስተው በምክክር በዘላቂነት መፍታት ወሳኝ ስለመሆኑ ተናግረዋል። ለዚህም ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ትልቅ ተስፋ የሰነቀ መሆኑን አንስተው ውጤታማ ሊሆን የሚችለው በችግሮቻችን ላይ መክረን ለመፍትሄው በጋራ መስራት ስንችል ነው ብለዋል።   ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አክሊለ ታጠቅ እና አቶ አብዶ ሙሜ፤ በለውጡ የመጡ ስኬቶችን ዘላቂ ለማድረግ ህብረ ብሄራዊ ሀገራዊ አንድነትን ማጽናት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በሀገር ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር የሚቻለው በችግሮቻችን ላይ መክረን የጋራ መፍትሄ መሻት ስንችል ነው ብለዋል።   ለዚህም ዜጎች ያለምንም ልዩነት ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ለትውልድ ግንባታ አደራ ተቀብለን መስራት ስንችል ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዘመናት እየተንከባለሉ የመጡ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር በመፍታት ለትውልዱ የምትመች ሀገር መገንባት ይቻላል በሚል መርህ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።    
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚኖራቸውን የክትትልና ድጋፍ ሚና አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል
Apr 9, 2026 3596
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፡-የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚኖራቸውን የክትትልና ድጋፍ ሚና አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሳበ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሟል።   በዚሁ ጊዜ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ እጸገነት መንግስቱ፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛል ብለዋል። ባለሥልጣኑም የሲቪል ማህበረሰብ የድርጅቶች ምዝገባና ቁጥጥር፣ ለሀገር ልማትና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚያበረክቱትን አስተዋፅኦ ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሕዊና ዴሞክራሲያዊነትም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላትም፤ ባለስልጣኑ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምዝገባና ክትትል የዲጂታላይዜሽን ሥርዓት ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራትን ጠይቀዋል። በተጨማሪም በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫና በሀገር የልማትና ዴሞክራሲ ባህል ግንባታ የበጎ ፈቃድ ሥራዎች ጋር የተያያዙ አስተያየትና ጥያቄዎችን አቅርበዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ፤ ሀገራዊ ለውጡ የፈጠረው ተቋማዊ የለውጥ እርምጃ ለሰቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንቅስቃሴ አስቻይ ሁኔታን ፈጥሯል ብለዋል። የባለስልጣኑ አገልግሎቶችን ሙሉ ለሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግ መታቀዱን አመልክተው፤ የተወሰኑ አገልግሎቶችን ወደ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የበጎ አድራጎት ስራዎችን ለማሳደግ ‘ቅን ልብ’ የተሰኘ መተግበሪያ ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚደረገውን ክትትል ለማጠናከር ውጤታማና ስጋትን መሰረት ያደረገ የመሰክ ምልከታ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ ከክልሎች ሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ምክር ቤቶች ጋር በጋራ እየተሰራ ነው ብለዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድርጅቶቹን ሚና ለማጎልበት እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችንም አብራርተዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ በበኩላቸው፤ ከምዝገባ ጀምሮ ወደ ስራ የተሰማሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚደረገው ክትትል ለማጠናከር የተሰሩ ስራዎቸን አብራርተዋል። የምክር ቤቱ የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እጸገነት መንግስቱ፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫው ሂደት ገለልተኛና ነጻ ሆነው በስፋት እንዲሰሩ የሚደረገው ክትትል ማጠናከር ያሰፈልጋል ብለዋል። ባለስልጣኑ በዲጂታላይዜሽንና በሰው ሀይል አቅም ግንባታ፣ የበጎ ፍቃደኝነት ስራዎችን ለማጎልበትና የምዝገባና ሂደቱን በጥንቃቄ ለማካሄድ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን አንስተዋል። ድርጅቶቹ በተቋቋሙበት ዓላማ መሰረት እየሰሩ መሆናቸውን እንዲሁም ጠንካራ አገሪቷን የሚመጥኑ ድርጅቶችን ለማስፋፋት መስራት ይገባል ብለዋል።  
ኢትዮጵያ እና ቡሩንዲ የተፈራረሟቸው የመግባቢያ ስምምነቶች ለቀጣናዊ ዘላቂ ልማት ያለውን የሀገራቱን የጋራ ቁርጠኝነት በይፋ የሚያረጋግጡ ናቸው
Apr 9, 2026 2407
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቡሩንዲ የተፈራረሟቸው የመግባቢያ ስምምነቶች ለቀጣናዊ ዘላቂ ልማት ያለውን የሀገራቱን የጋራ ቁርጠኝነት በይፋ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የቡሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንድያይሺሚዬ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተለያዩ የመግባቢያ ስምምነቶች ልውውጥ ላይ ታድመዋል። በመከላከያ፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በውሃና ኢነርጂ፣ በግብርና ፣ በንግድ ፣ በዲጂታል መታወቂያ እና በቱሪዝም ዘርፎች የተፈረሙት እነዚህ ሁሉን አቀፍ ስምምነቶች ለቀጣናዊ ዘላቂ ልማት ያለውን የጋራ ቁርጠኝነት በይፋ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። እነዚህ የመግባቢያ ስምምነቶች የሁለቱን ሀገራት ሰፊ አቅም በመደመር ወደ ብልጽግና ለምናደርገው የጋራ ጉዞ መሠረት የሚጥሉ እንደሆኑም ገልጿል።
የኢትዮጵያን ታሪካዊ ጠላቶች ፍላጎት ለማሳካት የታለመውን የጥፋት መንገድ በመተው የሰላም አማራጭ ተቀብለናል - ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን የቀድሞ አመራር አባላት
Apr 9, 2026 2365
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፡- ቀደም ሲል ሲከተሉት የቆዩት የጥፋት መንገድ አገርንና ሕዝብን የሚጎዳና የታሪካዊ ጠላቶችን ፍላጎት ለማሳካት ያለመ በመሆኑ የሰላም አማራጭ መቀበላቸውን ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን የቀድሞ አመራር አባላት ገለጹ። በጥፋት ቡድኑ ተታለው ጫካ የገቡ ወንድሞቻቸውም ወደ ሠላም አማራጭ እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል። እጃቸውን በሠላም ለመንግስት የሰጡ የጽንፈኛ ቡድኑ የቀድሞ አመራር አባላት ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ እስከአሁን ሲከተሉት የቆዩት መንገድ ለክልሉ ህዝብ አንዳች ጥቅም እንደሌለው በመረዳታቸው የሰላም አማራጭን ተቀብለዋል። በጫካ ቆይታቸው የተረዱት እውነታ "ለሕዝብ እንታገላለን" በሚል መፈክር ሽፋን የቀድሞ ሕወሃትና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ፍላጎት ለማሳካት የተጠለፈ ትግል መሆኑንና ሕዝብን ለጥፋት ለመዳረግ ያለመ አካሄድ መሆኑን ተገንዝበዋል። እጃቸውን በሰላም ከሰጡት ራሱን አፋብን ብሎ ከሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች መካከል የቀድሞ የኮር ፖሊት መምሪያ ኃላፊ ጌራወርቅ ዳኛው፤ የአማራ ሕዝብ ዘላቂ ተጠቃሚነት የሚረጋገጠው በሰላማዊ መንገድ መታገል ብቻ በመሆኑ ሰላማዊ አማራጭን ለመከተል ወስኛለሁ ብሏል። የጽንፈኛ ቡድኑ አመራሮች ከክልሉም ሆነ ከኢትዮጵያ ሕዝብ የልማት ፍላጎት በተጻራሪ በመቆም ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር ተባብረው ጥፋት በማድረስ ላይ ናቸው ያለው ጌራወርቅ፤ በማህበራዊ እሴቶችና መሰረተ ልማቶች ላይ በተደጋጋሚ የሚፈጸመው ጥቃት ከጀርባው የጥፋት ሴራ እንዳለው አመላካች መሆኑን ተናግሯል። ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን የቀድሞ አመራር አባል ሀምሳ አለቃ ፍቅሩ ሙልዬ በበኩሉ፤ የጽንፈኛው ቡድን አመራሮች ከሕዝብ ፍላጎት ይልቅ ለኢትዮጵያ ጠላቶችና ለግል ጥቅማቸው እየሰሩ መሆኑን ጠቁሟል። ለጽንፈኛው ቡድን የተለያዩ ጥያቄዎች ሲነሱ የትግል አጋርን በመፈረጅ የማሸማቀቅና አልፎም ሰበብ ፈልጎ የማስወገድ ተግባር እንደሚፈጸም አስረድቷል። እነርሱ ልጆቻቸውን ውጭ ልከው እያስተማሩ የደሃ ልጆችን ግን ለመስዋዕትነት እየዳረጉ ነው ሲል ሀምሳ አለቃ ፍቅሩ አብራርቷል። ሌላው የቡድኑ የቀድሞ አመራር አባል እና ኮር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር አየነው አስፋው እንደገለጸው፤ ራሱን አፋብን ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን አመራሮች ፍላጎት ትግሉን በማራዘም የራሳቸውን ሀብት ማካበት ላይ ማተኮር ነው። ለትግል በሚል የተጀመረው ዓላማ የሕዝብን የልማትና የእድገት ፍላጎት የሚያደናቅፍ፣ አንዳች ፋይዳ የሌለው መሆኑን መረዳቱን አመልክቶ፤ ለህዝብ ጥቅም እንቆማለን የሚሉት የጥፋት ቡድኑ አመራር አባላት ቤት በመስራት፣ ተሽከርካሪ በመግዛትና ሀብት በማካበት መጠመዳቸውን ገልጿል። በጥፋት በድኑ ራሱን የሸዋ ፋኖ ጠቅላይ ግዛት ብሎ የሚጠራው የቀድሞ ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ማንነገረው መለሰ እንደገለጸው፤ የግለሰቦችን የሥልጣን ፍላጎት ለማርካት የሚደረገው እንቅስቃሴ ሀገርን ከመጉዳት የዘለለ ፋይዳ የለውም። የቡድኑ አመራሮች ምንም ዓይነት ግልጽ ፖለቲካዊ እውቀት፣ መርህና ዝግጁነት የሌላቸው መሆኑን ጠቅሶ፤ ሕዝቡ የቡድኑን እውነተኛ ማንነት ሊገነዘብ እንደሚገባም አሳስቧል። ይህ አካሄድ ሕዝብም የማይደግፈው ውጤት የማያመጣ መሆኑን መረዳቱን ጠቅሶ፤ ሰላማዊ አማራጨ በመቀበል ለመጓዝ መምረጡን ተናግሯል። የመረጡት የሰላም አማራጭ የጥፋት ተልዕኮ ሳራዘም በክልሉ ሰላም ግንባታ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት እንደሆነ አስገንዝበዋል። በዚህም እኛ የሰላም አብሪ ሆነናል ያሉት የቀድሞው ጽንፈኛ ቡድን አመራር አባላት፤ በቀጣይም ቀሪ በጫካ የሚገኙ ወንድሞቻችን የመንግስትን የሰላም አማራጭ በመቀበል ለአማራ ህዝብና ለኢትዮጵያ ሰላም መስራት እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።
ማህበራዊ
በሐረሪ ክልል 250 አባወራዎችን ያካተተ ሞዴል መንደር ሊገነባ ነው
Apr 13, 2026 125
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል በገጠር ኮሪደር ልማት በቀጣይ ሁለት ወራት 250 አባዎራዎችንና እማወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሞዴል መንደር እንደሚገነባ የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ አስታወቁ። በክልሉ የገጠር ኮሪደር ዐቢይ ኮሚቴ ዕቅድ እና አፈጻጸም ላይ ውይይት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ርዕሰ መሥተዳድሩ እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት የተጀመረው የኮሪደር ልማት ከፅዱና ውብ አካባቢ ባለፈ ለዜጎች ምቹ የመኖሪያ ሥፍራ እንዲፈጠር እያስቻለ ነው።   በዚህም መሠረት በሐረር ከተማ በኮሪደር ልማት ዘርፍ የተመዘገበውን ውጤት በገጠሩ ክፍል ለማስፋት እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል። በገጠር አካባቢ የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎችም፤ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ሁኔታ ለመቀየር የሚያስችሉ መሆናቸውን ነው ያመላከቱት። ለአብነትም አርሶ አደሩ ያለውን ሀብትና ፀጋ በአግባቡ ተጠቅሞ ኢኮኖሚውን በማሳደግ በዚያው ልክ የተመቸ ኑሮ እንዲመራ የሚያግዝ መሆኑን ነው ያስረዱት። በክልሉ የሞዴል ገጠር መንደር መፈጠሩን የገለጹት ርዕሰ መሥተዳድሩ፤ ሞዴል መንደሩም ውኃና የኃይል አቅርቦትን ጨምሮ ሌሎች መሠረተ-ልማቶች እንዲሟሉ ተደርጓል ብለዋል። በቀጣይ ሁለት ወራትም 250 አባዎራዎችንና እማወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሞዴል የአርሶ አደሮች የመኖሪያ መንደር ለመገንባት ይሠራል ነው ያሉት። የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራ በላቀ ቁርጠኝነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠው፤ ለዚህም አርሶ አደሩ እያከናወነው የሚገኘውን የላቀ ተሳትፎና ድጋፍ እንዲያጠናክር አሳስበዋል። በየደረጃው የሚገኘው አመራርም ሥራዎችን በቅንጅት እና በትብብር እንዲሠራ ነው ያሳሰቡት። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የገጠር_ኮሪደር
ኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማብሰር የሚያስችሉ ተጨባጭ ተግባራትን እያከናወነች ነው
Apr 13, 2026 414
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም በመሸፈን የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማብሰር የሚያስችሉ ተጨባጭ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ እልፍ ጸጋዎች፣ እምቅ አቅሞች፣ ብሩህ ተስፋዎች፣ ተዝቀው የማያልቁ እሴቶችና ባለታሪክ ህዝቦች ያሏት ሀገር ናት፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ አቅሞቿና አንጡራ ሀብቶቿ ዜጎቿን ከድህነት ኢትዮጵያን ከተረጂ ሀገራት መደብ ሳያወጧት ዓመታት ነጉደዋል፡፡ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በስንዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ አሻራና በሌሎችም ሀገራዊ ጉዳዮች የተጀመሩ ኢኒሼቲቮች ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን እያመጡ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳብ አመንጪነት የሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም እሳቤ እየተተገበረ ነው፡፡ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ምንም ያልጎደላት ምንም ያላነሳት ሆና እያለ ለምን ተረጂ፣ ለማኝ ትሆናለች ከሚል ዕሳቤ የመነጨ ኢኒሼቲቭ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢኒሼቲቩ ተረጅነትና ጠባቂነት ወዴት እየወሰደን ነው ከሚል ቁጭት በመነሳት መጀመሩን ገልጸው፤ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ከመቻል ባለፈ የክብር የነጻነትና የሀገር ሉዓላዊነት ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ መንግሥት ተረጂነትን ለማስቀረትና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በግብርናው መስክ ተጨባጭ ለውጦችን ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም በመሸፈን የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማብሰር የሚያስችል የሚጨበጥ ተግባር እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የአደጋ ምላሽ ፈንድ በማቋቋም፣ የሎጂስቲክ ስርዓቱን በማሳለጥና ከውጭ የሚገባውን ስንዴ በማስቀረት ክልሎች የመጠባበቂያ ክምችታቸውን እያሳደጉ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ ለረጅም ዘመን እሴት ሆኖ የቀጠለውን የቤተሰብ ኃላፊነትና የማህበረሰብ አጋርነት ተቋማዊ ይዘት እንዲኖረው እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ 10 ክልሎች ሰብዓዊ ድጋፍን በራሳቸው አቅም መሸፈን መቻላቸውን የገለጹት ኮሚሽነሩ፥ አሁን ላይ ከውጭ የምናስገባው ስንዴ የለም ብለዋል። ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የጀመረችው ጉዞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አመራር ሰጪነት በከፍተኛ ተነሳሽነት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፤ በስኬታማ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
ሀገርን የማልማት ሥራ በበዓልና በእረፍት ቀናት ሳይገታ ተጠናክሮ ይቀጥላል 
Apr 12, 2026 1182
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 4/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገርን የማልማት ሥራ በበዓልና በእረፍት ቀናት ሳይገታ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ እየተገነባ በሚገኘው የኢንዱስትሪ ክላስተር የሥራ ቦታ በመገኘት በግንባታው ላይ ለሚሳተፉ ሠራተኞች ማዕድ አጋርተዋል።   ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ጊዜ፤ በተለወጠ የሥራ ባሕል በርካታ መሠረተ ልማቶች በጥራት እየተገነቡ መሆኑን ተናግረዋል። እየሰራን ሀገርን እየገነባን በዓልን እናከብራለን ያሉት ከንቲባዋ መስራት የሚያስከብር ተግባር መሆኑንና ከድህነት ለመውጣት በበዓል፣ በእረፍትም ሆነ በሌሊት ጠንክሮ መስራት የግድ እንደሚል አስገንዝበዋል። ይህ የኢንዱስትሪ ክላስተር ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት ለ13 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል። ግንባታውን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ሠራተኞች የበዓል ቀናትን ጨምሮ በከፍተኛ ተነሳሽነት እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል።   በዓል ምሉዕ የሚሆነው ከለውጥና ከብልፅግና ጋር ሲያያዝ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ የማዕከሉ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በአሁኑ ወቅት በመጠናቀቅ ላይ እንዳለ ገልጸዋል። ግንባታው ተጠናቆ ማዕከሉ ሥራ ሲጀምር ለበርካታ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ለውጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል። ሠራተኞቹ በበዓላትም ሆነ በእረፍት ቀናት ሳይወሰኑ ሀገርን ለማልማት እያሳዩ ላለው ትጋት ምስጋና አቅርበዋል። በግንባታው ላይ እየተሳተፉ ያሉት ሠራተኞች በሰጡት አስተያየት የተደረገላቸው የማዕድ ማጋራት የሥራ ተነሳሽነታቸውን እንደሚጨምረውና ለሀገር ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል። እንዲህ ያሉ የቅርብ ክትትልና ድጋፎች ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብና ጥራት እንዲጠናቀቅ ትልቅ አቅም እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
በዓላት ሲከበሩ የታመሙትን በመጠየቅ፣ የተቸገሩትን በመርዳትና አብሮነትን በማሳየት ሊሆን ይገባል
Apr 12, 2026 133
ባሕር ዳር፤ሚያዚያ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በዓላት ሲከበሩ የታመሙትን በመጠየቅ፣ የተቸገሩትን በመርዳትና አብሮነትን በማሳየት ሊሆን ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኀላፊ አብዱልከሪም መንግሥቱ ተናገሩ። የአማራ ክልል የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ባህር ዳር በፈለገ ሕይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመገኘት ታማሚዎችን በመጠየቅ ለታካሚዎች እና አስታማሚዎች ማዕድ አጋሩ።   በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኀላፊ አብዱልከሪም መንግሥቱ፤ ሆስፒታሉ የተሻሻለ እና ዘመናዊ የህክምና አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። የህክምና አገልግሎቱ እንዳለ ሆኖ በተለይም በዓላትን ስናከብር ታማሚዎችን አስታውሶ መጠየቅና አብሮነትን ማሳየት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም በዓላት ሲከበሩ የታመሙትን በመጠየቅ፣ የተቸገሩትን በመርዳትና አብሮነትን በማሳየት ሊሆን ይገባል ብለዋል። የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በሆስፒታሉ በመገኘት የታመሙትን መጠየቃቸውንና ማእድ ማጋራታቸውን ተናግረዋል። የፈለገ ሕይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሥራ አሥኪያጅ ዐቢይ ፍሰሐ በበኩላቸው፤ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ በሆስፒታሉ በመገኘት በመጠየቅና ማእድ በማጋራት አብሮነታቸውን በማሳየታቸው አመስግነዋል።   በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የሆስፒታሉ ቦርድ ሰብሳቢ ፍሰሐ ደሳለኝ፤ የበዓላት አከባበር በተለይም ማህበራዊ እሴቱ አብሮነት፣ መረዳዳትና መተጋገዝን መሰረት ያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም የትንሳኤ በዓልን ስናከብር የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳትና የታመሙትን በመጠየቅ መሆን ይኖርበታል ብለዋል።
ኢኮኖሚ
በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪዎች ለተኪና ወጪ ንግድ ምርቶች እድገት ትኩረት ተሰጥቶ ተከናውኗል
Apr 13, 2026 138
ባህርዳር፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአምራች ኢንዱስትሪዎች ለተኪና ወጪ ንግድ የሚውሉ ምርቶችን በዓይነትና በብዛት የማምረት ስራ ትኩረት ተሰጥቶት መከናወኑን የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ። መንግስት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ተግባራዊ በማድረግ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ያለውን ችግር በጋራ በመፍታት ዘላቂነት ያለው እድገትና ተወዳዳሪነት እንዲመዘገብ እያደረገ ይገኛል። በዚህም በርካታ ኢንዱስትሪዎች የመሰረተ ልማትና ሌሎች ችግሮቻቸው እየተፈታ የማምረት አቅማቸው እየጎለበተ ውጤታማ በመሆን ላይ ናቸው።   ኢንዱስትሪዎች ወጪ ምርቶችን እንዲሁም ተኪ ምርቶችን በራስ አቅም በማምረት የውጭ ምንዛሬ እጥረትን በማቃለል ለሀገር እድገት ያላቸው አስተዋጽኦ እየጨመረ የመጣበት ሁኔታ እየተፈጠረ ይገኛል ። ‎ከዚሁ ጋር ተያይዞ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅንቄ በመታገዝ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም እንዲጎለብት ተደርጓል። በወራቶቹ በንቅናቄው በተደረገ ጥረት 137 ከፍተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የውሃ፣ የመብራትና የመንገድ መሰረተ ልማቶች ተሟልተውላቸው ወደ ማምረት ሥራ ተሸጋግረዋል።   በአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና የኤክስፖርት ምርቶችን በዓይነትና በብዛት በማምረት ለሀገር እድገት ጥቅም ላይ ለማዋል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ‎በዚህም ከ554 ሺህ ቶን በላይ ተኪ ምርት በማምረት መንግስት ሊያወጣ የነበረውን 650 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል ብለዋል። ‎እንዲሁም በአምራች ኢንዱስትሪዎች የተመረተ 123 ሺህ ቶን ምርት ለውጭ ገበያ መቅረቡን ጠቅሰዋል። ‎በተጨማሪም ከ306 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ከ2ሺህ 925 በላይ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች ፈቃድ ወስደው ወደ ተግባር እንዲገቡ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። ‎ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ማምረት ሲሸጋገሩ ከ450 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩም አመላክተዋል። ‎በተቋሙ ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመተግበር የአገልግሎት አሰጣጡን ግልጽ፣ ፍትሃዊ፣ ምቹና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ‎በቀጣይም ቢሮው አምራች ኢንዱስትሪዎችን በልዩ ሁኔታ በመደገፍ ፈጥነው ወደ ማምረት ሥራ እንዲሸጋገሩና ወደምርት የገቡትም ምርታቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።
በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ለተሰማሩ ባለሀብቶች የገቢ ግብር ዕፎይታ ተፈቀደ
Apr 13, 2026 274
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ ግብዓትና ምርት ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሀብቶች ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑ በገንዘብ ሚኒስቴር ውሳኔ ተላለፈ። ሚኒስቴሩ ይህንን የፈቀደው የንግድ ቀጠናዎቹ ባለሀብቶችን ይበልጥ የሚስቡ እንዲሆኑ ለማድረግ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት በሚፈለገው መጠን እንዳያድግ ምክንያት ከሆኑት መካከል የካፒታል እጥረት፣ የግብዓት አቅርቦት ችግር እና የባለሙያ እጥረት በዋነኛነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ በመረጃው ጠቁሟል። በመሆኑም እነዚህን ችግሮች ደረጃ በደረጃ በማቃለል የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ልማትን ማሳደግ እንደሚገባ አስታውቋል። በዚህም መሠረት ግብዓቶች እና ሌሎችም ምርቶች በበቂ መጠን ለገበያ እንዲቀርቡ ለማድረግ፣ አስመጪዎች ምርቱን ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት የሚከፍሉት ቀረጥ እና ታክስ ውስን በሆነው ካፒታላቸው ላይ የሚያሳድረውን ጫና ማቃለል አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በነዚህ ምክንያቶች አስመጪዎች ግብዓቶችን እና ምርቶችን ቀረጥና ታክስ ሳይከፍሉ ወደ አገር አስገብተው፣ ለግብዓቱ ወይም ለምርቱ ገበያ ባገኙ ጊዜ ቀረጥና ታክሱን የሚከፍሉበትን አሰራር የሚፈቅድ የነፃ የንግድ ቀጣና አሰራር ተዘርግቷል። ይህንን ሥርዓት የሚያስፈጸሙ ነፃ የንግድ ቀጣናዎችም በየአካባቢው የተቋቋሙ መሆኑ ተመልክቷል። ይህንን ተከትሎም በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ ተሰማርተው ምርትና ግብዓት ለገበያ የሚያቀርቡ ባለሀብቶች ከላይ ከተጠቀሰው የታክስ አከፋፈል ስርዓት በተጨማሪ ከገቢ ግብር ነፃ እንዲሆኑ ተደርጓል። በመሆኑም ባለሀብቶች ይህንን ዕድል በመጠቀም በነፃ የንግድ ቀጣናዎች ውስጥ እንዲሰማሩ የገንዘብ ሚኒስቴር ጥሪውን አስተላልፏል።
በምዕራብ ሸዋ ዞን ለ2018/19 የምርት ዘመን የግብርና ግብዓቶች እየቀረቡ ነው
Apr 13, 2026 96
አምቦ፤ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የ2018/19 ምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ የማቅረብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ የኅብረት ሥራ ማህበራት ኤጀንሲ አስታወቀ። የኤጀንሲው ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት በላይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በምርት ዘመኑ የታቀደውን የሰብል ልማት ግብ ለማሳካት የተለያዩ የግብርና ግብዓቶች ከወዲሁ ለአርሶ አደሩ እየተሰራጩ ይገኛሉ።   በምርት ዘመኑ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለማሰራጨት ታቅዶ እየተሠራ ሲሆን፤ እስካሁን ከ461 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ በየወረዳው ለሚገኙ መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማህበራት ደርሷል ብለዋል። የማዳበሪያ አቅርቦቱ ለአርሶ አደሩ በዲጂታል አገልግሎት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይኸም ለፍትሐዊ ስርጭቱ እንደሚያግዝ አስታውቀዋል። በተመሳሳይ 8 ሺህ 244 ኩንታል ምርጥ ዘር ለማሰራጨት ታቅዶ፣ እስካሁን ከ2 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርጥ ዘር ቀርቧል ነው ያሉት። ይህ የግብዓት ስርጭት በዋናነት በአምቦ እና በቦረባኮ የገበሬዎች ዩኒየን በኩል እየተከናወነ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ ግብዓቶችም በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀርቡ አስታውቀዋል። ይህ ዝግጅት በዞኑ በመስኖና በመኸር የሚካሄደውን የሰብል ምርታማነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑንም አክለዋል። አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን ከማረጋገጥ ባለፈ፣ የኢኮኖሚ አቅሙን እንዲያሳድግና ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ተስማሚ የሆኑ ሰብሎችን እንዲያመርት አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ወይዘሮ መሰረት ገልጸዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የዞኑ አርሶ አደሮች ግብዓቶቹ በወቅቱ መድረሳቸው ለሥራቸው መሳካት ትልቅ እገዛ ማድረጉን ገልጸዋል።   አርሶ አደር ሀጫሉ ባይሳ፤ "በመጪው መኸር በቆሎና ሌሎች ሰብሎችን ለማልማት የሚያስፈልገንን ግብዓት አግኝተናል፤ አሁን ላይ መሬታችንን ደጋግመን በማረስ ለዘር ዝግጁ እያደረግን ነው" ብለዋል። ሌላው አርሶ አደር ወልደሰማያት ለታ፤ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በወቅቱ መድረሱ የእርሻ ሥራቸውን በጊዜ ለማቀላጠፍ እንደረዳቸው ጠቅሰው፣ በአምስት ሄክታር መሬታቸው ላይ በቆሎና ጥራጥሬ ለማልማት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።   ከዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በ2018/19 ምርት ዘመን በምዕራብ ሸዋ ዞን ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ይለማል።  
ከስደት ተመልሰን በተሰማራንበት የእንስሳት እርባታ ውጤታማ ሆነናል - ወጣቶች
Apr 13, 2026 140
አዳማ ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ በአርሲ ዞን የዴራ ከተማ ወጣቶች ከስደት ተመልሰው በተሰማሩበት የእንስሳት እርባታ ውጤታማ መሆናቸውን ገለጹ። ከስደት ተመላሾቹ መካከል ወጣት ሳዲቅ ሲራጅ እንደገለጸው በሕገወጥ መንገድ ባሕር አቋርጦ ዓረብ አገር ለረጅም ጊዜ ቢሠራም ውጤት አላገኘም።   ከስደት ሕይወቱ ትምህርት በመውሰድ በሀገሩ ሠርቶ የመለወጥ ዓላማን በመያዝ፣ መንግሥት ባመቻቸለት የሥራ ዕድል በመጠቀም በወተት ላሞች እርባታ መሰማራቱን ገልጿል። በዚህም የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸውን ላሞችን በግል መኖሪያ ቤቱ በማርባት የጀመረውን ሥራ በማሳደግ፣ ከዴራ ከተማ አስተዳደር በተረከበው በ350 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የወተት ላሞች እርባታ ማዕከል መገንባቱን አስረድቷል።   ይህም የወተት ምርቱን ለከተማዋ ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ እንዳስቻለው ጠቅሷል። ሌላኛው ከስደት ተመላሽ ወጣት ነቢዩ አብዱላሂ በበኩሉ፣ ከባለቤቱ ጋር ሠርተው መለወጥን በማሰብ በሕገወጥ መንገድ ዓረብ አገር በመሄድ ለዓመታት ያለ ውጤት ማሳለፋቸውን ያስታውሳል።   በስደት በቆዩበት ዓመታት ያጡትን ውጤት ሀገራቸው ሠርተው ለመለወጥ የመንግሥትን የሥራ ፈጠራ ዕድል መጠቀማቸውን ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅትም በማኅበር ተደራጅተው በዶሮ እርባታ ሥራ ላይ በመሰማራት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን ገልጸዋል። በዚህም 3 ሺህ የአንድ ቀን ጫጩቶችን በማስፈልፈል ለሌሎች ማኅበራት ማቅረባቸውን ተናግረዋል።   ሥራቸውን ለማሳደግም መንግሥት የዶሮ እርባታ ማዕከላትን ገንብቶ ከመስጠቱም ባለፈ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ብድር ማግኘታቸውንም ገልጸዋል። በሕገወጥ መንገድ ወደ ውጭ የሚጓዙ ወጣቶች ለአካል ጉዳትና ለሞት አደጋ ጭምር የሚጋለጡ በመሆኑ በሀገራቸው ሠርተው መለወጥ እንደሚቻል አስረድተዋል። የዴራ ከተማ ከንቲባ አቶ ኑራ ሁሴን በበኩላቸው አስተዳደሩ ከ300 በላይ የወተት ላሞችና የዶሮ እርባታ እንዲሁም የማድለቢያ ማዕከላት በመገንባት በማኅበር ለተደራጁ ወጣቶች በማስተላለፍ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።   በተለይ የከተማ ግብርናን ለማስፋፋትና ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በወተት ልማትና በዶሮ እርባታ እንዲሁም በማድለቢያ ሥራ የተሰማሩ ወጣቶች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ይገኛሉ ብለዋል። በከተማ ግብርና የተሰማሩ አንቀሳቃሾች ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን ከማሳደግ ባለፈ ለከተማዋ የገበያ መረጋጋት ማገዛቸውን ገልጸዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው
Apr 13, 2026 170
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። ዩኒቨርሲቲው ከስቴም (STEM) ማዕከል ጋር በመተባበር ባዘጋጀው አውደ ርዕይ ላይ፣ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ ዘርፎች ሥልጠና የወሰዱ የሮቤ ከተማ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የፈጠራ ሥራዎቻቸውንና ግኝቶቻቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት ረዳት ፕሮፌሰር ኢሳ ሐሰን እንደገለጹት፤ ተቋሙ የአካባቢውን ማኅበረሰብ ፍላጎትና ችግር መሠረት ያደረጉ ምርምሮችንና አገልግሎቶችን እያከናወነ ይገኛል።   ዩኒቨርሲቲው ከ"ስቴም ፓዎር" (STEMpower) ድርጅት ጋር በመተባበር ያቋቋመው ቤተ-ሙከራ፣ በዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በመፍታት ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል። ቤተ-ሙከራው ተማሪዎች በንድፈ-ሀሳብ የተማሩትን በተግባር እንዲለማመዱ በማድረግ፣ ሀገራዊና አካባቢያዊ ችግሮችን የሚፈታ ትውልድ ለመቅረጽ እያገዘ መሆኑን ጠቅሰዋል። የሮቤ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጀማል አባገሮ በበኩላቸው፣ አውደ ርዕዩ ተተኪው ትውልድ የፈጠራ አቅሙን እንዲያጎለብት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።   የስቴም ፓዎር ኢትዮጵያ የኦፕሬሽን ማኔጀር አቶ አንተነህ ፍሰሃ በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ" ስትራቴጂ አማካኝነት በሀገር ደረጃ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ አበረታች ለውጦች እየታዩ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አውደ ርዕይ የተማሪዎችን ዝንባሌ ከማሳደግ ባለፈ፣ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረውም አክለዋል።   በአውደ ርዕዩ ላይ የተሳተፉ ተማሪዎች በአካባቢያቸው የሚገኙ ቁሳቁሶችን በመጠቀም፣ ለችግር ፈቺ የሆኑ የቴክኖሎጂ ዲዛይኖችን አቅርበዋል። ተማሪዎቹ እንዲህ ያሉ መድረኮች ክህሎታቸውን ለማሳደግና ለወደፊት የፈጠራ ሥራዎቻቸው መነሳሳትን እንደሚፈጥሩላቸው ገልጸዋል። የሳይንስና ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ ነገም ቀጥሎ እንደሚውል ታውቋል።  
ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ያሳየችው ፈጣን ሽግግር እና ያስመዘገበችው ውጤት ለአህጉሪቱ  ምሳሌ ነው
Apr 10, 2026 432
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ያሳየችው ፈጣን ሽግግርና ያስመዘገበችው ውጤት ለአህጉሪቱ ምሳሌ መሆኑን በአፍሪካ ስታትስቲክስ ኢንስቲትዩት የኢኮኖሚ ስታትስቲክስ ዳይሬክቶሬት ኃላፊ አዱም ጋጎሉም ገለጹ። ኃላፊው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፣ ከአህጉሪቱ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 65 በመቶውን አስተዋጽኦ የሚያደርገውን መደበኛ ያልሆነ የኢኮኖሚ ዘርፍ ለመደገፍ ዲጂታላይዜሽን ወሳኝ ነው።   በኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን የፋይናንስ ተጠቃሚ ያደረጉት እንደ ቴሌ ብር እና ሲቢኢ ብር ያሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ ያመጡት ለውጥ እጅግ አስደናቂና አበረታች መሆኑን በምሳሌነት ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ለመክፈት የጀመረችው ስራ ለአህጉሪቱ አዲስ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑንም አንስተዋል። ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገችው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይም ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነትን ለማስፈን እንደ ቴሌኮም እና ባንክ ያሉ ቁልፍ ዘርፎች ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጋቸው የሀገሪቱን የሊብራላይዜሽን ጉዞ የሚያፋጥን ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብለዋል። የተመዘገቡት የልማት ስኬቶችና የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ በፈረንጆቹ 2063 የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚኖራቸው አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ እያሳየች ያለው ፈጣን ለውጥ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ከቀጠለ፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነትና ክብር ከፍ እንደሚያደርገው አብራርተዋል።   የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የስታትስቲክስ ዲፓርትመንት ምክትል ዳይሬክተር ጂም ቴብራክ፣ ዲጂታላይዜሽን የፋይናንስ ተደራሽነትን በማስፋት ለዓለም ኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።። በኢትዮጵያ በዲጂታላይዜሽን መስፋፋት እየታየ ያለው እንቅስቃሴ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በአሁኑ ወቅት ዓለም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘመን ላይ በመሆኗ፣ ሀገራት በጤና፣ በትምህርትና በንግድ ዘርፎች ተጠቃሚ ለመሆን አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል። ይህ የዲጂታል ለውጥ የፋይናንስ አገልግሎት ባልደረሰባቸው አካባቢዎች ጭምር ቀላልና ፈጣን አማራጮችን በማስፋፋት፣ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ነው ያብራሩት።
የክፍያ ስርዓቱ የትራንስፖርት ዘርፍ አገልግሎቱን በማዘመን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው
Apr 9, 2026 136
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮ-ቴሌኮም ያስጀመረው የክፍያ ስርዓት የትራንስፖርት ዘርፍ አገልግሎትን በማዘመን የሀገርን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑ ተገለጸ። ኢትዮ-ቴሌኮም "ቶሎ" የተሰኘ ዲጂታል የክፍያ ስርዓት ዛሬ አስጀምሯል።   የዲጂታል ክፍያ ስርዓቱ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ እና የኢትዮጵያ ክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሙስጠፋ አባሲመል በቱሉ ዲምቱ ዋና የክፍያ ጣቢያ አስጀምረዋል። የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ ተቋሙ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ አገልግሎቶችን ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮ-ቴሌኮም ከመደበኛ የቴሌኮም አገልግሎት ባሻገር ቀልጣፋ፣ ምቹና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት በማቅረብ የፋይናንስ ዘርፉን እየደገፈ መሆኑንም አስረድተዋል። በዚህም የሀገርን ልማት ዘላቂና አካታች ለማድረግ የዲጂታል መሰረተ ልማት ዝርጋታ ላይ ትኩረት በማድረግ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን ገልጸዋል። ኢንተርፕራይዙ በቀን ከ32 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ እንደመሆኑ፣ አዲሱ የ"ቶሎ" ዲጂታል ክፍያ አሠራር ጊዜን ከመቆጠብ ባሻገር የአገልግሎት ጥራትንና የመንገድ ደኅንነት ቁጥጥርን ማረጋገጥ የሚያስችል ነው። በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥር የሚገኘው ይህ ተቋም፣ አገልግሎቱን 100 በመቶ ዲጂታል ለማድረግና አረንጓዴ ኢነርጂን ተግባራዊ ለማድረግ እየሠራ እንደሚገኝም ተመላክቷል። ዛሬ የተጀመረው የዲጂታል ክፍያ መርሃ ግብርም የትራንስፖርት ዘርፉን አገልግሎት በማሳለጥ የሀገርን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማሳደግ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው ብለዋል። ይህም ደንበኞች ለዚሁ ዓላማ የተዘጋጀ ካርድ ተጠቅመው ክፍያ እንዲፈጽሙ የሚያስችል መሆኑ ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሙስጠፋ አባሲመል በበኩላቸው፤ ካሁን ቀደም ወረቀት መሰረት ያደረገ ክፍያ ስርዓት ይከናወን እንደነበረ ገልፀዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው፤ አገልግሎቱ ሙሉ ለሙሉ ዲጂታላይዝ የማድረግ ጉዞ ዛሬ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል። "ቶሎ" የተሰኘ የክፍያ ስርዓት ሶፍትዌር መልማቱን አመልክተው፤ ይህም ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ከቴሌ ብር ጋር በማስተሳሰር ዘመናዊ የክፍያ ስርዓት መጀመሩ አብስረዋል። በዚህም ደንበኞች የተዘጋጀውን ካርድ በመጠቀም ክፍያ እንዲፈፅሙ በማስቻል ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንደሚያገኙ ተናግረዋል። የክፍያ ስርዓቱ የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን ግልጽና የአሰራር ቅልጥፍና የሰፈነበት የዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው ብለዋል። ሁለቱ ተቋማት በቀጣይ አብሮ መስራት የሚያስችል የስምምነት ፊርማ ስነ-ስርዓት አካሂደዋል።
ዲጂታል ኢንሼቲቩ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት መፋጠን ያለው ፋይዳን በመገንዘብ በባለቤትነት መንፈስ ሊተገበር ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Apr 9, 2026 211
ባህርዳር፤ ሚያዚያ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሉ አመራር ዲጂታል ኢንሼቲቩ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት መፋጠን ያለው ፋይዳ በመገንዘብ በባለቤትነት መንፈስ ሊተገብረው እንደሚገባ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ አሳሰቡ። ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያና ኢትዮ ኮደርስ አፈጻጸም ያለበትን ሁኔታ በመገምገም ቀጣይ የስራ መመሪያ አስተላልፈዋል።   ርዕሰ መስተዳድር አረጋ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልእክት የመንግስት ተቋማትን አሰራር ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ የዲጂታል አሰራርን መተግበር ይገባል ብለዋል። በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያና ኢትዮ ኮደርስ ኢንሼቲቮች የዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑን የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። አመራሩም ኢንሼቲቮቹ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት መፋጠን ያላቸውን ፋይዳ በመገንዘብ በባለቤትነት መንፈስ ሊተገብራቸው እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የትምህርትና ጤና ሴክተር ሰራተኞችን ጨምሮ ሁሉም የመንግስት ሰራተኞች በዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው አመልክተዋል። የዲጂታል ትግበራው አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል፣ የዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥ፣ አለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማጎልበት በተሟላ ሁኔታ መተግበር አለበት ብለዋል።   በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው እየተተገበሩ የሚገኙት ኢንሸቲቮች የክልሉን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ የሚያፋጥኑ ሞተሮች መሆናቸውን ተናግረዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በርካታ ተቋማት በአንድ ማእከል አገልግሎታቸውን ለህብረተሰቡ በማቅረብ ይነሳ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር ለመቅረፍ ማስቻሉን አክለዋል። ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያን እስካሁን 5 ነጥብ 3 ሚሊዮን የክልሉ ነዋሪዎች መውሰዳቸውን ጠቁመው፤ በቀጣይ ሦስት ወራትም ቀሪ ግቦችን ለማሳካት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።   የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ባንችአምላክ ገብረማሪያም፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የኢትዮ ኮደርስና የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ለማሳካት እንደሚያስችሉ አስረድተዋል። በመድረኩ ላይ ዘርፎቹን የሚመሩ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ስፖርት
አርባምንጭ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ተጋሩ 
Apr 13, 2026 170
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት አርባምንጭ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ፍፁም ጥላሁን በ29ኛው እና ተገኑ ተሾመ በ36ኛው ደቂቃ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ቅዱስ ጊዮርጊስ መሪ ሆኗል። ናይጄሪያዊው ጄሮም ፍሊፕ በ42ኛው እና ሴኔጋላዊው ማማዱ ሴክ በ97ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፏቸው ግቦች ለአርባምንጭ ከተማ ወሳኝ አንድ ነጥብ አስገኝተዋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ የ2 ለ 0 ውጤቱን ማስመዝገብ አልቻለም።   ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ32 ነጥብ ደረጃውን ከ15ኛ ወደ 12ኛ ከፍ አድርጓል። ቡድኑ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ማስመዝገብ አልቻለም።   አርባምንጭ ከተማ በ23 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል። በሀዋሳ ከተማ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሜዳ ውሃ በመያዙ፣ በሀዋሳ ከተማ እና በምድረ ገነት ሽሬ መካከል ሊደረግ የነበረው የምሽት 12 ሰዓት ጨዋታ በዳኞች ውሳኔ ሳይካሄድ ቀርቷል። የሊጉ አክሲዮን ማህበር የመርሐ ግብሩን አዲስ የጨዋታ ቀን እና ቦታ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ገልጿል። ዛሬ በተደረጉ የ27ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች መቀሌ 70 እንደርታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 ሲረታ ሸገር ከተማ እና ነገሌ አርሲ አንድ አቻ ተለያይተዋል።
በወራጅ ቀጠና የሚገኘው መቀሌ 70 እንደርታ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አገኘ
Apr 13, 2026 137
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር መቀሌ 70 እንደርታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፍፁም አለሙ እና ኮትዲቯራዊው አብዱላጢፍ ባምባ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ግብ አስቆጣሪው ኮትዲቯራዊው አብዱላጢፍ ባምባ በ82ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ወጥቷል። ዳዊት ገብሩ ለወልዋሎ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው መቀሌ 70 እንደርታ በ26 ነጥብ 19ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ላለመውረድ በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። በሊጉ ያስመዘገባቸውን ድሎች ብዛትም ወደ አምስት ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በሊጉ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ29 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ወልዋሎ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ከ142 ሚሊዮን በላይ ችግኞች እየተዘጋጁ ነው
Apr 13, 2026 126
ጎንደር፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ከ142 ሚሊዮን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች የማዘጋጀት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን አጠናክሮ በማስቀጠል የአካባቢውን ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው።   ለዚህም በዞኑ ሥር ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች በተቋቋሙ 12ሺህ የችግኝ ጣቢያዎች ከ142 ሚሊዮን በላይ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውና የአካባቢውን ስነ ምህዳር ለመጠበቅ የሚያግዙ ችግኞች እየፈሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኞቹ በመጪው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የሚተከሉ መሆናቸውን ገልጸው፣ እስካሁን በተደረገ ጥረትም ቀድመው የሚፈሉ 76 ሚሊዮን ሀገር በቀል ችግኞችን በማፍላት የእንክብካቤ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   በክረምቱ ከሚተከሉ ችግኞች ውስጥ ከ40 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የሚሰጡ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ቡናና መሰል የፍራፍሬ ችግኞች እንደሆኑም አስረድተዋል። እንደ አቶ ንጉሴ ገለጻ፣ በመጪው ክረምት 33ሺህ ሄክታር የሚሸፍን የችግኝ ተከላ ሥራ ለማከናወን የቦታ መረጣና ሌሎች ዝግጅቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአካባቢን ስነ ምህዳር ከማስጠበቅ ባለፈ በርካታ ወጣቶች በግላቸው ችግኝ አፍልተው በመሸጥ የሥራ ዕድል እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም አያይዘው ገልጸዋል።   የዞኑ ህብረተሰብ ችግኝ የተተከለባቸውን ቦታዎች ከመከለል ባለፈ በራሱ ወጪ ሠራተኞችን ቀጥሮ የእንክብካቤና የጥበቃ ሥራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ ባለፈው ዓመት ክረምት ከተተከሉ 121 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 86 በመቶው ጸድቀዋል ብለዋል። የደን ልማት ሥራ ለግብርና ሥራችን መሰረት በመሆኑ በየዓመቱ በክረምት ወራት ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የወገራ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር በላይነህ ስጦታው ናቸው፡፡ የጎንደር ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ ወጣት አምሳሉ ገነቱ በበኩሉ እንዳለው እሱና ጓደኞቹ በማህበር ተደራጅተው ባቋቋሙት የችግኝ ጣቢያ ሀገር በቀል የዛፍና የፍራፍሬ ችግኞችን አፍልተው ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እየሆኑ መጥተዋል፡፡   ለመጪው ክረምትም ከ500 ሺህ በላይ ችግኞች በማፍላት ለገበያ ለማቅረብ እየተዘጋጁ መሆኑን ጠቁመው፣ ከችግኞቹ መካከል ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የአቮካዶ እና የማንጎ ዝርያዎች ይገኙበታል ብለዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አሁናዊ የደን ሽፋን መጠን 15 ነጥብ 2 በመቶ መድረሱን ከዞኑ ግብርና መምሪያ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የፖለቲካ ቁርጠኝነትና የሕብረተሰብ ንቁ ተሳትፎ የታየበት በአፍሪካ ቀዳሚ ኢንሼቲቭ ነው
Apr 9, 2026 108
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፡-የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የፖለቲካ ቁርጠኝነትና የህብረተሰብ ንቁ ተሳትፎ የታየበት በአፍሪካ ቀዳሚ ኢንሼቲቭ መሆኑን የብሄራዊ አረንጓዴ አሻራ የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) ገለጹ። ኢትዮጵያ የምታስተናግደው 16ኛው የአፍሪካ አደጋ ሥጋት አቅም አህጉራዊ ጉባኤ "ለሉዓላዊነት መተባበር" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን እየተካሄደ ነው።   የአፍሪካ አደጋ ሥጋት አቅም አባል ሀገራትና ታዛቢዎች እንዲሁም የዘርፉ ተዋንያን የሚሳተፉበት ጉባኤው በአፍሪካውያን መካከል ትብብርና አጋርነትን በመፍጠር አህጉራዊ የአደጋ ሥጋትን የመከላከልና የፋይናንስ አቅምን ማጠናከርን ያለመ ነው። ጉባኤው የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም፣ ለአደጋ ስጋት ምላሽ ለመስጠት እና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ አፍሪካ መር መፍትሔ ማፈላለግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ምክክርና የጋራ መግባባት መፍጠር ያስችላል። የብሄራዊ አረንጓዴ አሻራ የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በመድረኩ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያስመዘገበችውን ስኬትና ለአፍሪካ ያላትን ተሞክሮ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የመጀመሪያ ምዕራፍ 50 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ስታቅድ በወቅቱ ምሁራን ሳይቀሩ ዕቅዱ ሊሳካ አይችልም የሚል ጥርጣሬ እንደነበራቸው አስታውሰዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እሳቤ መሆኑን ጠቅሰው፤ የተራቆተ መሬትን እንዲያገግም ማድረግ ሥነ-ምህዳሩን መመለስ እና ለግብርናና ከተማ ልማት ምቹ ከባቢ መፍጠር ነው ብለዋል። በዚህም የተለያዩ ሀገር በቀል እና ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ ችግኞችን በመትከል የኢትዮጵያን ምድር አረንጓዴ ማልበስ መጀመሩን ገልጸዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከቀጣይነት ያለው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃን በማጠናከር የግብርና ሥራዎች ምቹ ሥነ-ምህዳር መፍጠሩን ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ የመላው ኢትዮጵያውያንና ተቋማት ትብብር የጋራ ውጤት ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ ከጠቅላይ ማኒስትሩ ጀምሮ የሁሉም አመራር ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ጠቅሰው፤ ለጎረቤት ሀገራት ጭምር ተሞክሮ ሆኗል ብለዋል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ተቀባይነት ማግኘቱን ገልፀው፣ ኬንያ በአስር ዓመት ውስጥ 15 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ተሞክሮ መውሰዷን ተናግረዋል።  
ለአየር ንብረት ለውጥ የማትበገር አፍሪካን ለመገንባት አህጉራዊ አንድነታችን ወሳኝ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Apr 9, 2026 217
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፡- ለአየር ንብረት ለውጥ የማትበገር አፍሪካን ለመገንባት አህጉራዊ አንድነታችን ወሳኝ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ በሰው ልጅ መገኛዋ ኢትዮጵያ፣ በአፍሪካውያን መሰባሰቢያ አዲስ አበባ፣16ኛውን የአፍሪካ የሥጋት መከላከል ዐቅም ጉባኤ (ARC-COP16) በይፋ አስጀምረናል ብለዋል።   አህጉራችን በአየር ንብረት ለውጥ ክፉኛ እየተፈተነች ትገኛለች ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ ሆኖም ይህ ፈተና ተስፋችንን የሚያጨልም፣ ጉዟችንን የሚገታ አይሆንም ሲሉም ገልጸዋል። በእልህ፣ በቁጭትና በእንችላለን ኅብረት አንድነታችንን የምናጠናክርበት አጋጣሚ ነው። እኛ አፍሪካውያን ከአደጋ በኋላ ለሚመጣ ርዳታ እጅ ከመዘርጋት ይልቅ፣ አደጋን ቀድሞ መከላከልና በሳይንሳዊ መንገድ ለመፍትሔ መዘጋጀት የህልውናችን መሠረት ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ ራዕይ ሰንቃ፣ ክንዷን አበርትታ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ዐቅም እየገነባች መሆኑን ገልጸው፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የምድርን ገጽታ እየቀየርን መሆኑንም ተናግረዋል። በምግብ ሉዓላዊነት ንቅናቄ ራሳችንን ለመቻል እየተጋን ነው። በታዳሽ ኃይል ልማትም የአህጉራዊ ትሥሥር ገመድ እየሆንን ነው ብለዋል። ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች በበዙበት፣ በአንጻሩ ዓለም አቀፋዊ ድጋፎች በቀነሱበት በዚህ ወቅት፣ የአፍሪካ ሥጋትን የመከላከል ዐቅም (African Risk Capacity-ARC) የመሰሉ አህጉራዊ ተቋሞቻችንን ማጠናከር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑንም ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው የአደጋ ሥጋትን በጥናት መለየት፣ ቀድሞ መከላከል፣ ችግር ሲከሠትም በአፍሪካዊ ዐቅም ምላሽ መስጠት ይገባል። ኢትዮጵያም ለዚህ የአፍሪካውያን ሌላኛው የሉዓላዊነት ግብ መሳካት በአርአያነት ትተጋለች ብለዋል።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ለአፍሪካ ምሳሌ ናቸው
Apr 8, 2026 556
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ፣ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከልና ምላሽ ለአፍሪካውያን ምሳሌ የሆኑ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት 16ኛው የአፍሪካ አደጋ ሥጋት አቅም አህጉራዊ ጉባኤ "ለሉዓላዊነት መተባበር" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን እየተካሄደ ነው።   39 የአፍሪካ አደጋ ሥጋት አቅም አባል ሀገራትና ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን እየተሳተፉበት የሚገኘው ይህ ጉባኤ፤ በአፍሪካውያን መካከል ትብብርና አጋርነትን በመፍጠር አህጉራዊ የአደጋ ሥጋትን የመከላከልና የፋይናንስ አቅምን ማጠናከርን ያለመ ነው። የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካውያን የምግብ ሉዓላዊነትን በራሳቸው አቅም ለማረጋገጥ ለጋራ ግብ የሚተባበሩበት ወሳኝ ወቅት ላይ ናቸው፡፡ የአፍሪካ የአደጋ ሥጋት አቅም አህጉራዊ የምግብ ሉዓላዊነትን በራስ አቅም ለማሳካት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ የተቀናጀ የአደጋ ሥጋት ምላሽ መስጠት የሚያስችል አህጉራዊ የፋይናንስ አቅም መገንባት ይገባል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ግቦችን በማሳካት የምንመኛትን አፍሪካ ለመገንባት የሀገራት ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነትና ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ስርዓት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ቀዳሚ አጀንዳ መደረጉን ገልጸው፤ ጠንካራ ተቋማዊ አደረጃጀት በመፍጠር የተሟላ ድጋፍ ማድረግ የሚያስችል አቅም ተገንብቷል ብለዋል፡፡   ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ አረንጓዴ አሻራ፣ መስኖ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የታዳሽ ኃይል እና ሌሎችም ኢንሼቲቮች የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን በመከላከል እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን በመመከት፣ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥና የአደጋ ምላሽ በመስጠት ለአፍሪካና ለዓለም ምሳሌ እየሆነች ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ያሳየችው ስኬት ጉባኤውን ለማስተናገድ ተመራጭ እንዳደረጋትም ኮሚሽነሩ አንስተዋል። የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም ጉባኤ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም በማሟላትና የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ያስመዘገበቻቸውን ተሞክሮዎች የምታጋራበት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ሥርዓት ለመገንባት የተገበረቻቸው ኢኒሼቲቮች የምግብ ሉዓላዊነትን እና የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ማሳካት እንደሚያስችሉ ተናግረዋል፡፡ በአዲስ አበባ የሚሰሩ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን መከላከልና የአደጋ ምላሽ በመስጠት ለአፍሪካውያን ምሳሌ የሆኑ የተግባር ማሳያዎች ናቸው ብለዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 404
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ሊቀ መንበርነትን ተረከበች
Apr 3, 2026 318
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የእ.አ.አ አፕሪል 2026 የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት (AU PSC) ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነትን በይፋ መረከቧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ ሊቀ መንበርነቱን የተረከበችው ከኮትዲቯር ነው። ኢትዮጵያ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የምክር ቤቱን አጀንዳዎች በሊቀመንበርነት መምራት እንደምትጀምር ሚኒስቴሩ አመልክቷል። በዚህም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2025 በድጋሚ የምክር ቤቱ አባል ሆና ከተመረጠች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀ መንበር መሆን ችላለች። በሊቀመንበርነት ቆይታዋ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ በሚገኙ አገራዊ እና ወቅታዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን እንደምትመራ ሚኒስቴሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያን ሊቀ መንበርነት በይፋ ለማብሰር እና አዲስ የተመረጡ የምክር ቤቱን አባላት ለመቀበል መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰብሳቢነት የሰንደቅ ዓላማ የማውለብለብ ሥነ-ሥርዓት ይከናወናል። ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2004 ምክር ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በአባልነት ስታገለግል የቆየች መሆኑን የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፤ እ.አ.አ በ2025 በድጋሚ ለሦስት ዓመታት አባል ሆና መመረጧን አውስቷል። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም አራት ጊዜ የምክር ቤት አባል ሆና ተመርጣ በንቃት ስትሳተፍ መቆየቷ ተወስቷል።
ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል
Mar 28, 2026 607
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስገነዘቡ። 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው እየተሳተፋ የሚገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነው የአለም የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ውስጥ የአባል ሀገራቱን ጥቅም የሚያስከብር ጠንካራ ድርጅት ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም በአፅንኦት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው ለድርጅቱ ጥንካሬ ይበጃሉ ያላቸውን ሀሳቦችም አካፍለዋል። በዚህም ድርጅቱ የብዙኃነት አቅም ያለው በመሆኑ ይህን አቅም ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ማምጣት ያስፈልጋል ነው ያሉት።   ለዚህም የደቡብ - ደቡብ ግንኙነትን ማጠናከር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ያሉ ሲሆን መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚን ከገነቡ ሀገራትና ድርጅቶች ጋር ያለን ግንኙነት ከቀደመው የእርዳታ ሰጭ እና ተቀባይ ግንኙነት ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የድርጅቱ አባል ሀገራት ተመሳሳይ የባለቤትነት ስሜትን ማዳበር እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል። ቀጣይነት ያለው ልማት ማረጋገጥ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባትና ሰላምና ፀጥታን ለማስፈን መስራት የአባል ሀገራት የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት አባል ሀገራት ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ያላቸው ሚና ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት(አምራችነት) መሸጋገር እንዳለበትም ተናግረዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ጉዳይ በልዩ ትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ባስመዘገበቻቸው ውጤቶች ቀጣዩን የአለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመርጧን አስታውሰዋል። ይህም የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት በመገንባት ሂደት ያላቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበት ትልቅ ዕድል እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል።   የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በበኩላቸው ሶስቱም ቀጣናዎች የጎላ አስተዋጽኦ ባላደረጉበት የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገዱ መሆናቸውን አንስተዋል። የአየር ንብረት ፍትህ እንዲረጋገጥ የተባበረ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በጉባኤው አፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ክልሎችን የወከሉ መሪዎች ንግግር ያደረጉ ሲሆን አፍሪካን በመወከል የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ኤቫሪስት ንድዪሺሚዬ መልእከት አስተላልፈዋል። የድርጅቱን የፋይናንስ ምንጭ ቀጣይነት ማረጋገጥ፣ የድርጅቱን መዋቅራዊ አሰራር ማጠናከር እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ አቋም መያዝ በጉባኤው ጎልተው የተሰሙ ድምፆች መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። በማላቡ ኢኳቶሪያል ጊኒ እየተካሄደ የሚገኘው 11ኛው የአፍሪካ፣ ካርቢያን እና ፓስፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ እስከ ነገ መጋቢት 20/2018 ዓም ድረስ ይቆያል። በጉባኤው ከሶስቱም ክልሎች የሚገኙ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው 
Mar 22, 2026 301
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሐተታዎች
በኢዜአ ዐይን …!
Apr 13, 2026 137
በምግብ ራስን የመቻል ጉዞ አንዱ ምሰሶ - የስንዴ ልማት በሙሴ መለሰ ስንዴ በኢትዮጵያ በከፍትኛ ደረጀ ከሚመረቱና ለግብይት ከሚውሉ የሰብል ምርቶች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የስንዴ አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል በግንባር ቀደምነት ትጠቀሳለች። ከ2011/2012 የምርት ዘመን በፊት ኢትዮጵያ በመኸር የምታለማው ስንዴ ከ1 ነጥብ 7 ሚሊየን ሔክታር ያልበለጠ ነበር። የበጋ መስኖ ስንዴ ሲጀመርም 3 ሺህ ሔክታር ብቻ እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በመኸር፣ በበጋ መስኖ እና በበልግ ወቅት 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ እያለማች እንደምትገኝ የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያስረዳል። ሚኒስቴሩ የ2018 ዓ.ም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፤ 4 ነጥብ 29 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ ስንዴ በማልማት ከበጋ መስኖ ስንዴ 175 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን መግለጹ ይታወሳል። በኢትዮጵያ በአብዛኛው የስንዴ ምርት የሚመረተው በአነስተኛ አርሶ አደሮች ነው። ባለፉት ዓመታት ግን የሜካናይዝድ እርሻ የስንዴ ምርቱን በእጥፍ እንደጨመረው ይገለጻል። መንግሥት መስኖን በመጠቀም ስንዴን በዓመት አንድ ጊዜ ከማምረት ወደ ሦስት ጊዜ ማምረት የሚቻልበትን አሰራር በመፍጠር የሀገሪቱን ምርታማነት ለማሳደግ እየሠራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ107 ሚሊየን ኩንታል በላይ ነው። ይህንን ፍላጎቷን ለመሙላት ለዓመታት ከ700 ሚሊየን ዶላር እስከ 1 ቢሊየን ዶላር ለስንዴ ግዥ ወጪ ታደርግ ነበር። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ትሸፍን የነበረውም ከውጭ በምትገዛው ስንዴ ነበር። መንግሥት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በማስፋፋትና በየዓመቱ የሚመረትበትን ዙር በመጨመር ኢትዮጵያ የስንዴ ፍጆታዋን ሙሉ በሙሉ እንድትሸፍን በትኩረት ሲሠራ ቆይቷል። በዚሁ በ2014 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገር ስንዴ ማስገባት አቆመች። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያገኘችው ውጤት ከውጭ ማስገባትን ማስቆም ብቻ አልነበረም። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ራስን ብቻ ሳይሆን ኤክስፖርት የማድረግ ዐቅም እንዳላት በመግለጽ፤ ስንዴ ወደ ውጪ መላክ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስቀመጡት ሀገራዊ ግብ መሰረት ኢትዮጵያ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ውጭ የመላክ ተግባርን በይፋ አስጀምራለች። የስንዴ ኤክስፖርቱ ኢትዮጵያ ገጽታዋን የሚለውጥ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ መግባቷን የሚያመላክት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ገልጸው ነበር። ኢትዮጵያ በ2015 ዓ.ም የሀገር ውስጥ ፍጆታዋን ሸፍና 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ለውጭ ገበያ የማቅረብ ዐቅም እንዳላት ብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚና የኤክስፖርት ኮሚቴ አረጋግጧል። ኮሚቴው የሀገራዊ የነፍስ ወከፍ ፍጆታና የሀገሪቱን አጠቃላይ የምርት ሚዛን በማጥናት ከፍጆታ የሚተርፍ 32 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ ወደ ውጭ መላክ እንደሚቻልም ተገልጿል። 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ባሳለፍነው የካቲት ወር በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄዱ የሚታወስ ነው። በወቅቱም የአፍሪካ ሕብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ከጉባዔው ጎን ለጎን በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ ተምሳሌታዊ የሆነ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ የስንዴ ምርታማነቷን በማሳደግ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈን ባለፈ ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሏን ሕብረቱ መመልከት መቻሉንም ተናግረዋል። የአፍሪካ ሀገራት በዓመት ውስጥ ለምግብ ምርቶች ከሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ ስንዴ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዝም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከውጭ የሚገባውን ምርት በሀገር ውስጥ ስንዴ መተካት እንደሚቻል በተግባር ያሳየችበት መንገድ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የኢትዮጵያን ተሞክሮ ወስደው ወደ ተግባር እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ሥራ ላይ እያሳየች ያለውን ሥራ አስፍታ ከቀጠለች በምግብ ራሷን የመቻል ሕልሟን የማሳካት እድሏ ሰፊ መሆኑንም ማመላከታቸው ይታወሳል።
የጤና ነገር ...
Apr 3, 2026 2123
በዮሐንስ ደርበው የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። የኒውትሬሽን ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ የሰው ልጅ የሰውነት ክፍል 60 በመቶው ውኃ እንደመሆኑ ለተስተካከለ ጤና ሚዛን መጠበቅ በቂ ውኃ መጠጣት ይገባል። ውኃን በትክክለኛው መጠንና ጊዜ መውሰድ ከተቻለ የኩላሊት ህመም ተጋላጭነትን 50 በመቶ መቀነስ እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ነገር ግን ሰውነት የሚፈልገውን የውኃ መጠን በአግባቡ ካላገኘ ለዕለታዊ እና በጊዜ ሂደት ሥር ለሚሰድዱ ህመሞች የመጋለጥ ዕድል እንደሚጨምርም ያነሳሉ። ለመሆኑ ሰውነት የሚፈልገውና በቂ የውኃ መጠን የሚባለው መጠኑ ስንት ነው? በቂ ውኃ አለመጠጣትስ የሚያስከትለው ችግር ምንድን ነው? በሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎች ላይ የኒውትሬሽን መምህር፣ ተመራማሪ እና ደራሲ ይሁኔ አየለ ምላሽ አላቸው። አንድ ሰው የሚያስፈልገው የውኃ መጠን በዕድሜ፣ ጾታ፣ በሥራ ባሕርይ፣ በመኖርያ አካባቢ፣ እንደ ጤና ሁኔታው እና እንደ ሰውነት ክብደቱ እንደሚወሰንም በምላሻቸው አስገንዝበዋል። ለምሳሌ የስኳር ታማሚዎች፣ የምታጠባ እናት፣ በዕድሜ የገፉ ሰዎች፣ ብዙ አድካሚና ላብ የሚያወጡ፣ በሞቃታማ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች በቀን 3 ሊትር ውኃ መጠጣት አለባቸው ይላሉ። በአማካይ ግን በቀን አንድ ሰው ከ2 እስከ 3 ሊትር ውኃ መጠጣት እንደሚጠበቅበት ይገልጻሉ። ጤናማ ሕይወት የሚመሠረተው ከውኃ ነው፤ ለምሳሌ ውኃማውን 60 በመቶ የሰውነት ክፍል ሚዛን ለማስጠበቅ የግድ አስፈላጊውን መጠን ውኃ መጠጣት እንደሚገባ ይመክራሉ። በሰውነት ውስጥ የሚካሄደው ሕይወታዊ ሂደት (ባዮሎጂካል ፕሮሰስ) ውኃን መሠረት ያደረገ መሆኑን አስገንዝበው፤ ለምሳሌ ለተስተካከለ የሥርዓተ-ምግብ ሂደት፣ ቆሻሻን ከሰውነት አጣርቶ ለማስወጣት፣ የአጥንት መገጣጠሚያ ሥራን ለማስተካከል እና ለሌሎችም በርካታ የሰውነት ክፍሎች የተሳለጠ ተግባር ውኃ ቁልፍ መሆኑን አንስተዋል። ይህን ተከትሎም ውኃ ካሎሪ አልባው መድኃኒት (ተፈጥሯዊው መድኃኒት) እስከመባል መድረሱን ነው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ያስረዱት። ሰውነት የሚያስፈልገውን ያህል ውኃ አለመጠጣት ግን ድካም ያስከትላል፤ ለማየት፣ ለመንቀሳቀስ፣ ለመሥራት፣ ለማሰብ፣ ለመረጋጋት . . . አያስችልምና ሲሉ ያብራራሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንድ ሰው ውኃ የመጠማት መጠኑ ከአራት በመቶ በላይ ከሆነ ለሞት ሊጋለጥ እንደሚችልም ጠቅሰዋል። ውኃ አለመጠጣት፤ የጨጓራ ህመምን በማባባስ ማስገሳት፣ የቆዳ ድርቀትና ግርጣት፣ የኩላሊት ህመም ሌሎች የሰውነት ክፍሎችም ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሠሩ ያደርጋል ነው ያሉት። ከምግብ በፊት 30 ደቂቃ ቀድሞ ውኃ መጠጣት ውፍረትን ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል። በቂ ውኃ ከመጠጣት በተጨማሪ ፍራፍሬዎችንና አትክልቶችን ማዘውተር እንደሚመከርም ገልጸዋል። የፈላ ውኃ እና የዝናብ ውኃን በብዛት መጠጣት በሰውነት ውስጥ ያሉ ንጥረ ነገሮችን በማስወገድና በኩላሊት ላይም ጫና እንደሚፈጥር አመላክተዋል። ለተስተካከለ ጤናማ ሕይወት የግድ ውኃ መጠጣትን ልማድ ማድረግ እንደሚገባም ይመክራሉ። #ውኃ_መጠጣት #ጤና #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency
ከሀገራዊ ለውጡ አበርክቶዎች
Apr 3, 2026 2228
በዮሐንስ ደርበው የለውጡ መንግሥት ኢትዮጵያን ማሥተዳደር ከጀመረ እነሆ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ላይ 8 ዓመት ሞላው። በእነዚህ ዓመታት በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚው፣ በማኅበራዊ ዘርፉ በዲፕሎማሲውና በሌሎችም መስኮች የተለያዩ ስኬቶች ተከናውነዋል። በእነዚህ ጥቂት ዓመታትም ለማሳካት ቀርቶ ለማሳብ የማይደፈሩ ብዙ ውጤቶችም ተመዝግበዋል። የተገኙት ስኬቶች ከጊዜያቸው የፈጠኑ ናቸው። ለዚህም ሕዝቡ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በነቂስ እየወጣ አድናቆቱን ገልጿል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሰጡት የሰላ አመራርነትና ቁርጠኝነትም አክብሮቱንና ምሥጋናውን ገልጿል። የለውጡ መንግሥት አካሄድ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የልማት ፕሮጀክቶችም በይበልጥ ተስፋፍተውና ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መንግሥት ለሚያደርገው ጥረት ከጎኑ እንደሚቆሙም በድጋፍ ሰልፍ ላይ ባስተጋቧቸው መልዕክቶቻቸው አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ በለውጡ መንግሥት ለማሳካት ቀርቶ ለማሰብ የማይደፈሩ ተግባራት ተከናውነዋል። ከእነዚህ ከፍተኛ ጥቅም ከተገኘባቸው የታሪክ እጥፋትን ካሠረጹ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል ጥቂቶቹን ቀጥለን በወፍ በረር እንዳሥሣለን። ከመጋቢት ሥጦታዎች መካከል - የጉባ ብሥራቶች ሥልጣኔ - በምርጫ ካርድ መምረጥ የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! የዘርፉ ባለሙያዎች ‘ካሎሪ አልባው መድኃኒት’ ይሉታል። • የኮሪደር ልማት እንደምናውቀው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነትና ልዩ ትኩረት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከሁሉም አስቀድሞ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ ነው። አሁን ላይ ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የበርካታ ከተሞችን ገጽታ የቀየሩ አስደማሚ ሥራዎች ተከናውነውበታል። ይህም በገጠር ጭምር ተጠናክሮ የቀጠለ ጉዳይ ነው። ለዘመናት አሮጌ ገጽታዋን ይዛ ያሸለበችውን አዲስ አበባ እንደ አዲስ የፈጠራትም ይኸው ፕሮጀክት ነው። አሁን ላይ መዲናይቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባን ለውጥ ዐይተው ዝም ማለት አልቻሉም። ከመደመማቸው አንጻር የዘወትር አጀንዳቸውም እያደረጓት ይገኛሉ። ይህንን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት፤ ኮሪደር ልማት ማለት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት ነው ማለታቸው ይታወሳል። ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑንንም አስረድተዋል። ከለውጡ መንግሥት ዐበይት የትኩረት መስኮች አንዱ የሆነውን የቱሪዝም ዘርፉን እንቅስቃሴ ለማሳደግም ቁልፍ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ ድርብርብ ፕሮጀክት ነው የኮሪደር ልማት። • የበጋ መስኖ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የለውጡ መንግሥት ዋነኛ ትኩረቱ ነው። ለዚህም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን አንዱ ማሳኪያ ሥልት አድርጎ እየተጋ ይገኛል። የበጋ መስኖ ስንዴ ኢትዮጵያ ስንዴን ከውጭ ማስገባት አቁማ መላክ እንድትጀምር ያስቻለ ኢኒሼቲቭ ነው። በዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችና በሜካናይዜሽን ታግዞ በስፋት እየተሠራበትም ይገኛል። ከለውጡ መንግሥት ወዲህ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ምክንያት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በምርታማነት ማደግና የሥራ ዕድል በመፍጠር አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብም ከፍተኛ ውጤት ተገኝቶበታል። ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ ስንዴ ላይ ባሳየችው ትጋት፤ ፍጆታዋን በራሷ ዐቅም የሸፈነችው፣ ስንዴን ከውጭ ማስገባትን ያቆመችው፤ ስንዴን ወደ ውጭ መላክ የጀመረችው በለውጡ መንግሥት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ በመሸለም ለጥረታቸው ዕውቅና መስጠቱም ይታወሳል። • መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀደም ሲል አንድ ጉዳይን ለማስፈጸም እዚያም እዚህም መንከራተት የግድ ነበር። በዚህ አያበቃምና ወረፋውም ሌላ ችግር ነው። መንግሥት በተለያዩ መድረኮች ባካሄዳቸው ሕዝባዊ ውይይቶች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉልን የሚሉ እሮሮዎች በረከቱ። መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል ሥራ ወደ ተግባር አሥገባ። በዚህም መሠረት ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ ጀመረ። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነውም አሉ። ለዚህ ቁርጠኝነታችን አንዱ ማሳያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመራቸውንም ገለጹ። እንግዲህ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ አንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ ታግዘው በተሳለጠ ሂደት እንዲሰጡ በማድረግ የተገልጋይን እንግልት፣ ገንዘብ እና ጊዜ መቀነስ ያስቻለ አሠራር ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት ተደርጎም ይወሰዳል። በየከተሞቹም እየተስፋፋ ነው። • አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ አይ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ተጠቃሚ እንድትሆን ከፍተኛ ጉጉት እንዳላቸው በቁጭት በተለያዩ መድረኮች ያነሳሉ። ለዚህም መፍትሔ ዘይደው ተቋማትን ከማቋቋም ጀምሮ ለዘርፉ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ ተግተዋል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂው ጋር አብሮ ለመጓዝ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን አቋቋመች። የኤ አይ ዩኒቨርሲቲ በመክፈት በግብርናው፣ በጤናው እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠርም በሂደት ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት ቀይሮ ወደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ሕንፃ በተዛወረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአምስት ዓመት ውስጥ አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ መድረሱ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ የሮቦቶችን ሶፍትዌር ብቻ ሳይሆን ውጫዊ የአካል ክፍልን (ሃርድዌር) መሥራት ጀምሯል ብለዋል። ድሮን ማምረት ብቻ ሳይሆን የማነጋገር ዐቅም እየፈጠረ ያለ ተቋም መሆኑንም አንስተዋል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ደረጃ የሚወዳደር አሠራርን የሚከተል መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ምርቶችን አውጥቷል ማለታቸው ይታወቃል። ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮሉሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን ሲሉ ማስገንዘባቸውም ይታወሳል። • የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው። በዚህ ሂደት ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊታአውራሪነት ይጠቀሳል። በተደራጀና ተቋማዊ ሆኖ ባልተቆራረጠ አካሄድ እየተከናወነ ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተተከሉ ችግኞችም በየዘርፉ ተጠቃሚነት አድጓል፤ ተጠናክሮም ይቀጥላል። • የሌማት ትሩፋት ከመጋቢት ሥጦታዎች አንዱ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ነው። የምርት አቅርቦትን በማስፋት ለተረጋጋ ግብይት እና ለተመጣጠነ ሥርዓተ-ምግብ ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከት ላይም ይገኛል። ኢኒሼቲቩ ለግብርና ኢንቨስትመንትና ለሀገራዊ የሥርዓተ-ምግብ መሻሻል ጉልኅ ሚና እየተጫወተ ነው። የዋጋ ንረትን በማረጋጋት፣ የምርት ስብጥርን በማሳደግና በዘላቂነት በማቅረብ ረገድም የጎላ ሚና አለው። የግድ ሰፋፊ መሬት መፈለግ ሳያሻ በትንሽ ቦታ ብዙ በማምረት ፍጆታን ከመሸፈን አልፎ ኢኮኖሚን በመደጎም እና የሥራ ዕድል በመፍጠርም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው። • የቱሪስት መዳረሻ ልማት ቅርሶች እንዲጠገኑ፣ አዳዲስ ሎጂዎች እንዲገነቡ፣ በመዳረሻ ስፍራዎች መሠረተ-ልማት እንዲሟላ ያስቻሉ ተግባራት በለውጡ መንግሥት ተከናውነዋል፤ አሁንም ተጠናክሮ የቀጠለ እና ስኬታማ ኢኒሼቲቭ ነው። በዚህ ሂደት ከሐሳብ አመንጭነት ባሻገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የጻፉትን መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ ጭምር ለቅርስ ጥገናና ለቤተ-መጻሕፍት ግንባታ እንዲውል አድርገዋል። በተጨማሪም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት፤ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ ወደ ተግባር አስገብተዋል። በእነዚህ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። አማራጭ የቱሪስት መዳረሻም ሆነዋል። • የተቋማት ግንባታ ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል መሪል ሐሳብ በተካሄደው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ፤ የተቋማት ግንባታና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ብለዋል። በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ሲሉም አስገንዝበዋል በወቅቱ። ዘመን የማይለውጣቸው ዘላቂ ጠንካራ ሃገራዊ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ብዙ ርቀት መጓዝም ተችሏል። በመሆኑም የመንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲሆኑ በማድረግ እና ሥርዓት በተለዋወጠ ቁጥር የማይፈርሱ ወይም የሚሻገሩ ተቋማት መገንባት ተችሏል። ይህ ትጋት ተጠናክሮም ቀጥሏል።
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3734
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … በኢዜአ ዐይን …! የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 11, 2026 146
ከመጋቢት 27 እስከ ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦ • ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ የትንሣኤ በዓል በክርስቲያኖች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው በዓል ነው፤ ሞት የተሻረበትና ሕይወት ዋስትና ያገኘበት ነው ብለዋል። የትንሣኤ በዓል ከሞት ባሻገር ሕይወት ከመቃብር ባሻገር ትንሣኤ መኖሩ የታወጀበት መሆኑንም ገልፀው፤ ሞት መጨረሻ መቃብር መዳረሻ አለመሆናቸው የተረጋገጠበት ነው ብለዋል በመልዕክታቸው። የዘንድሮውን ትንሣኤ የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በሚያልፍ ፈተና ውስጥ እንዳለች እያሰብን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን ሲሉ ገልፀዋል። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ በጥልቁ ጨለማ ጠፍተን እንድንቀር አሥረው ለመያዝ የሚሞክሩ ወጥመዶች ብዙ ናቸው፤ ወደ ተስፋ ምድር እንዳንሻገር የሚጎትቱ ሰበቦች ሞልተዋል፤ ዳሩ ግን ከሕማማቱ ወዲያ ትንሣኤ ከዕንቅፋቱ ባሻገር ስኬት እንደሚጠብቀን አምነን እንታገላለን ሲሉም አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ትንሣኤ መቃረቧን ገልፀው፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ከሚበሰርባቸው ምዕራፎች አንዱ ግንቦት ላይ የሚካሄደው ምርጫ መሆኑንም አመላክተዋል። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም ብለዋል። • የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሁለት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ካደረጉት የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት ኢቫሪስቴ ንድያይሺሚዬ ጋር ውጤታማ የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን ባሳለፍነው ሳምንት ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ለማጠናከር ያለሙ በርካታ የመግባቢያ ሰነዶች ፊርማ አከናውነናል ሲሉም አስታውቀዋል። ስምምነቶቹ ለሁለቱም ሀገራት የበለጸገ እና የተባበረ መጻኢ ዕድልን የሚያረጋግጡ የቆዩ ግንኙነቶቻችንን ወደ ተጨባጭ ትብብር ለመቀየር እንደ ወሳኝ መሠረት የሚያገለግሉ የጋራ ቁርጠኝነታችን ማሳያ ጭምር ናቸው ብለዋል። ጉብኝታቸውን እንዳጠናቀቁም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው ሸኝተዋቸዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪኤግዚም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኢሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም ስትራቴጂካዊ ግንኙነታችንን በምናጠናክርባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረናል ብለዋል። • የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሥተዳደር ዓመታዊ አፈጻጸም ግምገማ ባሳላፍነው ማክሰኞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሥተዳደር ፕሬዚዳንት ሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦላቸው በውጤቶቹ ላይ ግምገማ እና ውይይት አድርገዋል። • የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ሹመት መራዘም በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 62(9) እና በዐዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀፅ 2(ለ) መሠረት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አሥተዳደርን በርዕሰ መሥተዳደርነት እንዲመሩ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አሥተዳደር አስመልክቶ በጸደቀው ደንብ ቁጥር 479/2013 አንቀጽ 4(2) እና የዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ባቀረቡት መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደን ሹመት ለአንድ ዓመት አራዝመዋል። • ማዕድ ማጋራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች እና ጽሕፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሕጻናት ማዕድ አጋርተዋል። • የአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ኅልፈተ ሕይወት አምባሳደር ቆንጅት፤ በዲፕሎማሲው መስክ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ላበረከቱት ጉልኅ አስተዋጽዖ፣ ለሰጡት አስተምኅሮና ለነበራቸው ብልኅ አመራር ምንጊዜም ሲታወሱ እንደሚኖሩ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባስተላለፉት የኀዘን መግለጫ መልዕክት ገልጸዋል። ትጉኅና ከብረት የጠነከሩ ዲፕሎማት ነበሩ በማለት ለሙያቸው የነበራቸውን ጽኑ አቋምና የሀገር ፍቅር ስሜትም አንስተዋል። ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት በማረፋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሰማቸውን ኀዘን ገልጸዋል። አምባሳደሯ ለሕግ፣ ለአሠራር፣ ለፕሮቶኮል እና ለኢትዮጵያ ጥቅሞች በነበራቸው የጸና አቋም እናስታውሳቸዋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከእርሳቸው በኋላ አያሌ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል ብለዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባስተላለፉት የኀዘን መግለጫ መልዕክት፤ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ እና ታላቅ ዐሻራን ማሳረፍ የቻሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ጥልቅ ኀዘን ተሰምቶኛል ብለዋል። አምባሳደር ቆንጂት እስከ ከፍተኛ ዲፕሎማትነት በደረሰ ረጅም የሥራ ዘመናቸው ለሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ያስመዘገቡት ድል እና ያበረከቱት አስተዋጽዖ ሁልጊዜም በክብር የሚታወስ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ባሳለፍነው ሳምንት “ፖሊሳዊ አንድነት ለዘላቂ ሰላም” በሚል መሪ ሐሳብ 20ኛው የፖሊስ ኮሚሽነሮች መክፈቻ ጉባዔ ተካሂዷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፤ የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያ ፖሊስ በሚሰጠው አገልግሎት ታማኝም አሳማኝም መሆን አለበት ብሎ ያምናል ብለዋል። የፖሊስ ኃይላችን የጥፋት ኃይሎች በሀገራችንና በሕዝባችን ላይ የሰነዘሩትን ጥቃት በአንድነት በመቆምና መስዋዕትነት በመክፈል ቀልብሷል፤ ይህም ለሁላችንም ኩራት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የፖሊስ አመራሮችና የሠራዊቱ አባላት በዕውቀት፣ በታማኝነትና በሕዝብ አገልጋይነት ሥነ-ልቦና ለላቀ ተልዕኮ እንድትዘጋጁ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
ከፓን አፍሪካኒዝም እስከ ኢኮኖሚያዊ አጋርነት - የኢትዮጵያ እና ብሩንዲ የስድስት አስርት ዓመታት የዲፕሎማሲ ጉዞ
Apr 9, 2026 454
በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያና የብሩንዲ ግንኙነት የሚጀምረው አፍሪካ ከቅኝ አገዛዝ ቀንበር ለመውጣት በምትታገልበት ወሳኝ ወቅት እንደነበረ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። ኢትዮጵያ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌት እንደመሆኗ፣ ብሩንዲ እ.ኤ.አ በ1962 ከቤልጂየም ቅኝ አገዛዝ ወጥታ ነፃነቷን ስታገኝ ግንኙነታቸውን በይፋ ከጀመሩ የመጀመሪያዎቹ አገራት ተርታ ትመደባለች። ይህ ግንኙነት በወቅቱ በነበረው የፓን-አፍሪካዊነት መንፈስ እና አፍሪካዊ መፍትሄ ለአፍሪካዊ ችግሮች በሚለው መርህ ላይ የቆመ ነበር። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ምስረታ ላይ የነበራቸው የጋራ ተሳትፎ ለዘመናት ለዘለቀው ወንድማማችነት ጠንካራ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጧል። ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ አዳዲስ ከቅኝ ግዛት ነፃ የሚወጡ የአፍሪካ ሀገራትን ወደ አህጉራዊው መድረክ ለማምጣት በነበራቸው ራዕይ መሰረት፣ ከብሩንዲ የመጀመሪያው ንጉሥ ምዋሚ ምዋቡትሳ አራተኛ ጋር የጠበቀ ግንኙነት መስርተዋል። ግንኙነቱ በይፋ ከተጀመረ ከአንድ ዓመት በኋላም (እ.አ.አ 1963) ብሩንዲ በአዲስ አበባ በተመሰረተው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) ላይ በመስራች አባልነት እንድትሳተፍ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ድጋፍ አድርጋለች። በወቅቱ የነበረው የሀገራቱ ግንኙነት በፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል እና በቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ የተመሰረተ ነበር። በወቅቱ ይደረጉ በነበሩ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ስብስባዎች ላይ ኢትዮጵያ እና ብሩንዲ አህጉራዊ አጀንዳዎችን በጋራ አንጸባርቀዋል። ኢትዮጵያ በብሩንዲ የሰላም ሂደት ውስጥ ትልቅ ሚና ተጫውታለች። በተለይም በብሩንዲ የነበረውን የእርስ በርስ ጦርነት ለማስቆም በተደረገው ጥረት እና በአፍሪካ ህብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (AMIB) ውስጥ የኢትዮጵያ ሰራዊት ቀዳሚ ተሳትፎ ነበረው። ልዑኩ በአፍሪካ ህብረት ታሪክ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ በአህጉሪቱ የተመራና የተደራጀ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንደሆነ ይወሳል። ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ እና ከሞዛምቢክ ጋር በመሆን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት ልካለች። ሰራዊቱ የተኩስ አቁም ስምምነቱ እንዲከበር ማድረግ፣ ታጣቂዎችን ትጥቅ ማስፈታት እና ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረግ (DDR) ላይ ትልቅ ስራ ሰርቷል። ኢትዮጵያ በወታደራዊ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በዲፕሎማሲው ረገድም ንቁ ተሳትፎ አድርጋለች። የአሩሻ የሰላም ስምምነት እንዲሳካ እና በብሩንዲ የሽግግር መንግስት እንዲመሰረት በወቅቱ የነበሩ የኢትዮጵያ መሪዎች በኢጋድ (IGAD) እና በአፍሪካ ህብረት በኩል ጫና ሲያደርጉና ሲያሸማግሉ ቆይተዋል። በብሩንዲ በተለያዩ ቡድኖች መካከል እምነት እንዲገነባ ኢትዮጵያ እንደ ገለልተኛ እና ታማኝ አደራዳሪ ትታይ ነበር። ተልዕኮው ስራውን አጠናቆ ወደ ተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (ONUB) ሲቀየርም የኢትዮጵያ ሰራዊት እዛው በመቆየት ለሰላሙ ዘላቂነት አስተዋፅኦ ማድረጉን ቀጥሏል። ይህም ኢትዮጵያ ለቀጣናዊ ሰላም ያላትን ቁርጠኝነት አሳይቷል። ይህም በሁለቱ ሀገራት ትብብር ውስጥ በትልቁ የሚነሳ እና የሚወሳ ነው። በፓን አፍሪካኒዝም እና በፖለቲካዊ ወዳጅነት ላይ መሰረት አድርጎ የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ተለያዩ መስኮች እየሰፋ መጥቷል። እ.አ.አ በ1970ዎቹ መጀመሪያ በሀገራቱ መካከል የተፈረሙ የንግድ እና የባህልን ትብብር የማጠናከር የጋራ መግባቢያ ሰነዶች የዚሁ ማሳያ ናቸው። ባለፉት ዓመታት በሀገራቱ መካከል የተደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እና የጋራ ስብሰባዎች ግንኙነቱን ከማጠናከር ባለፈ የትብብር አድማሱን ማስፋትን ከግምት ውስጥ ያስገቡ መሆናቸውን ማየት ይቻላል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እ.አ.አ በ2023 በብሩንዲ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ በኢትዮጵያ እና ብሩንዲ መካከል ያለውን የኢኮኖሚ፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ አቪዬሽን እና ቀጣናዊ ሰላም ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ነው። በጉብኝቱ ወቅት ብሩንዲ የኢትዮጵያን የስንዴ ልማት እና የአረንጓዴ አሻራ ተሞክሮ በስፋት ለመተግበር ያላትን ፍላጎት አሳይታለች። የሁለትዮሽ ውይይቱ የተለያዩ ውጤቶች የተገኙበት ነው። በሁለቱ ሀገራት መካከል የንግድ ልውውጥን የሚያቀላጥፉ ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ ውሳኔ ተላልፏል። ኢትዮጵያ ለብሩንዲ በቴክኒክ እና በሙያ ስልጠና (TVET) ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብታለች። የሀገራቱ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን (JMC) በየጊዜው እየተገናኘ ስምምነቶችን እንዲከታተል መመሪያ ተሰጥቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከውይይቱ በተጨማሪ ግብርና እና ኢንዱስትሪን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2023ቱ የብሩንዲ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በማጠናከር ረገድ በዋና ማሳያነት የሚጠቀስ ነው። የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ እ.አ.አ በ2021 በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በጉብኝቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለብሩንዲ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ችግኞችን በስጦታ አበርክተው ነበር። ይህም ሀገራቱ በግብርና እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ያላችውን ፍላጎት የሚያሳይ ነበር። በፕሬዝዳንቱ ጉብኝት ወቅት የመጀመሪያ የኢትዮ-ብሩንዲ የመጀመሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባ ተደርጓል። በወቅቱ በግብርና፣ በቱሪዝም እና በትምህርት ዘርፍ አዳዲስ የመግባቢያ ሰነዶች ተፈርመዋል። እ.አ.አ በ2023 የብሩንዲ ፓርላማ የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን (CFA) በህግ አፀደቀ (Ratified)፤ ይህም ለኢትዮጵያ ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል ተደርጎ ተቆጠረ። ኢትዮጵያ ብሩንዲ ስምምነቱን እንድታጸድቅ ድጋፍ አድርጋለች። ይህም የሀገራቱን የውሃ ትብብር የበለጠ ያጸና ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከብሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የቀድሞው የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ፒዬር ንኩሩንዚዛ እ.አ.አ በ2012 በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል። ይህም በሀገራቱ የከፍተኛ አመራሮች የጉብኝት ልውውጦች ውስጥ የሚጠቀስ ነው። ከንኩሩንዚዛ ጉብኝት ሁለት ዓመታት በኋላ እ.አ.አ በ2014 ብሩንዲ በኢትዮጵያ ኤምባሲዋን ከፍታለች። ይህም የሀገራቱን ትብብር ለማጠናከር የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው። ኢትዮጵያ ከብሩንዲ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ስራ የሚሸፍነው በካምፓላ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ነው። ኢትዮጵያ እና ብሩንዲ በተለያዩ ጊዜያት ተደራራቢ ታክስን ማስቀረት፣ በኢንቨስትመንት፣ አየር ትራንስፖርት፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በመከላከያ እና ፀጥታ፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲሁም ባህልና ስፖርት ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶች ተፈራርመዋል። ጉብኝቶችና ስምምነቶች ኢትዮጵያና ብሩንዲ ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ትብብር በማሳለጥ እና የጋራ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድ ያላቸው ሚና ወሳኝ ነው። ሁለተኛው የኢትዮጵያና የብሩንዲ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን (Joint Ministerial Commission - JMC) መጋቢት 29 እና 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሄዷል። ስብስባውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ፣ የቀጣናዊ ትስስርና የልማት ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና በጋራ መርተውታል። በተጨማሪም የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና የዘርፍ ባለሙያዎች ተገኝተዋል። በስብስባው ማብቂያ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶች ተፈርመዋል። ስምምነቶቹም በዋናነት በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር (በተለይም በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ)፣ በግብርና ምርታማነት፣ በአቪዬሽን እና በቀጣናዊ ደህንነት ዙሪያ ላይ ያተኮሩ ናቸው። ስብስባው የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠናን (AfCFTA) መርህ መሰረት በማድረግ የሁለቱን ሀገራት የኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር፣ የመሰረተ ልማት ግንኙነቶችን ማስፋፋት እና በአባይ ተፋሰስ የጋራ ተጠቃሚነት ዙሪያ ተቀራርቦ ለመስራት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ሰነድ በመፈረም በስኬት ተጠናቋል። ውይይቱ የኢትዮጵያ እና የብሩንዲን ትብብር የበለጠ ማጠናከር የሚያስችል ነው። የቡሩንዲ ፕሬዝዳንትና የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸው የሁለቱን ሀገራት ትብብር ከማጠናከር ባለፈ በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትስስር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። የኢትዮጵያ እና የብሩንዲ መጻኢ የሁለትዮሽ ትብብር በሁለገብ ዘርፎች ላይ ያተኮረና ወደ ላቀ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚሸጋገርበት ወቅት እንደሚሆን ይጠበቃል። የፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ጉብኝት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽኑ ውሳኔዎች፣ ለቀጣዮቹ ዓመታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ለሚኖረው ጠንካራ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ትስስር መጠናከር ጉልህ ሚና ይኖረዋል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 4, 2026 1147
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 20 እስከ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ስለ አዲስ አበባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ አዲስ አበባ ከዋና ከተማ በላይ መሆኗን ገልጸው፤ በፈጣን እንቅስቃሴ ላይ ያለች፣ ወደ ኢትዮጵያ ነገ የመግቢያ በር፣ በፍጥነት እየተለወጠች ያለች የሀገር የልብ ትርታ፣ ሁሉንም አሳታፊ እና አርቆ አሳቢ የሆነ የከተማ ልማት ትልማችን መገለጫ ናት ብለዋል። ፈጣን መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት፣ የዘመናዊ ከተማ መፍትሔዎችን በማቅረብ፣ አካታች በሆነ መልኩ መኖሪያ ቤት በመገንባት እና ዘላቂ ዕድገትን በማረጋገጥ እየሠራን ያለነው ዛሬን ብቻ ሳይሆን ለነገው ትውልድ ጭምር ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ የሚገኙ ከተሞቻችን ሰዎችን ለማብቃት፣ ዐቅምን ለመጠቀም እና ዘላቂ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ ቅርጽ ይዘዋልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። • አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መርቀው ከፍተዋል። ‎በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው ብለዋል በወቅቱ። ‎የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን እንዲሁም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከል ማከተቱን አብራርተዋል። ‎ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። • የአዲስ ስፖርት ፓርክ መመረቅ ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)‎ የከተማችንን እድሳት ለማፋጠን እና የዜጎቻችንን ክብር ለመመለስ የገባነውን ቃል አንዱ ማረጋገጫ የሆነውን የአዲስ ስፖርት ፓርክን በይፋ መርቀን ከፍተናል ብለዋል። ‎በ5 ነጥብ 7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ፕሮጀክት፤ በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ 15 አትሌቶችን የሚዘክሩ የክብር ሐውልቶችን በፓርኩ መሃል በማቆም፣ የጀግኖቻችን ታሪክ ለተተኪ ትውልድ ስፖርተኞች ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋልም ነው ያሉት። የኦሎምፒክ ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ኳስ፣ የቅርጫት ኳስና የሜዳ ቴኒስ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የ800 ሜትር የሩጫ ትራክን ጨምሮ፤ እያንዳንዱ የዚህ ማዕከል ክፍል የዓለም አቀፍ መስፈርቶችን እንዲያሟላ ተደርጎ ተገንብቷል ሲሉም ገልፀዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በአፋር ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፋር ክልል ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት በአዋሽ ወንዝ ተፋሰስ በመሥኖ እየለማ ያለው የሱፍ ምርት ለተሻገረ ግብርና እና ለተሻገረ ገጠር ራዕያችን ተደማሪ ሃብት ነው ብለዋል። በአፋር ክልል ያየነው በመሥኖ ተፋሰስ በረሃ የመሰለውን ምድር የምርት መትረፍረፊያ የማድረግ ትጋት፤ ለሌሎች በተለይም ከዓመት እስከ ዓመት ዝናብ አጠር አካባቢዎች ትልቅ የመማሪያ ሠነድ እንደሚሆን አመላክተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በተካሄደው "የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ቅንጅት ለሀገራዊ ሰላም እና ደኅንነት" በሚል መሪ ሐሳብ በተካሄደው ብሔራዊ የደኅንነት ኮንፈረንስ ላይ የተሳተፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፤ በዚሁ ወቅት ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች የጸጥታና ደኅንነት ተቋሞቻችን ችግርን ወደ ዕድል እንዲቀየሩ ያስቻሉ ናቸው ብለዋል፡፡ ጉዟችን ተጀመረ እንጂ አልተቋጨምና ከትናንት ዕዳዎች ተላቀን፣ የዛሬ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን ለነገው ትውልድ የምትመጥን ሀገር ለመገንባት በዓላማ ጽናት እንቀጥላለን ሲሉም አመላክተዋል። • ስለ መጋቢት 24 መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ወደ ሥልጣን የመጣውን የለውጡን መንግሥት የሚደግፉ ሕዝባዊ ሰልፎች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተካሂደዋል። በእነዚህ ሰልፎች ላይም መንግሥት ባለፉት ሥምንት ዓመታት ያመጣቸውን ለውጦች እና የተገኙ ስኬቶችን የሚያወሱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም (ዶ/ር) ለሰጡት ስኬታማ አመራርነት የሚያሞግሱና የሚያመሠግኑ መልዕክቶች ተስተጋብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ቀኑን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሕዝባዊ ግፊትና ትግል ያመጣው የመጋቢት ለውጥ ኢትዮጵያን ወደ ኋላ ያስቀሩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ስብራቶችን መጠገን ያስቻሉ ሪፎርሞች የተተገበሩበት ነው ብለዋል። ለሕዝባችን የላቀ ተጠቃሚነት፣ ለሀገራችን ክብርና ብልፅግና መሳካት አበክረን እንሠራለን ሲሉም ገልጸዋል። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በበኩሉ ቀኑን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በኃይልና በምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ አስደማሚ ስኬቶችን አስመዝግባለች ብሏል። የለውጡን መሠረት ከማስፋትና ከማጽናት ወደ ማላቅ የተሸጋገረችው ኢትዮጵያ፤ በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌትነቷን በተግባር ታውጃለች ሲልም ገልጿል። ይህን ለውጥ ዕውን ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ፤ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በድል እንደሚያሳርጉት ጥርጥር የለውም ነው ያለው። • የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ስምምነት የኢትዮጵያ መንግሥት በInvest in Ethiopia 2026 ፎረም፤ ከቻይና፣ ፖላንድ፣ ሕንድ፣ ሲንጋፖር እና ኬንያ ከመጡ አጋሮች ጋር የ13 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ታሪካዊ የኢንቨስትመንት ስምምነት መፈራረሙን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት አስታውቋል። በታዳሽ ኃይል፣ በማዕድንና በአረንጓዴ አሞኒያ ዘርፎች ላይ ያተኮሩት እነዚህ ስምምነቶች፤ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችን ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ጉልህ ማሳያ ናቸው ብሏል። በተመሳሳይ ጽሕፈት ቤቱ ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለውን የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ የሚተካ የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 ሆኖ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል ብሏል። የ1954 የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕጉ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየ በመሆኑ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግሥት እና ከወንጀል ፍትሕ ፖሊሲ እንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በዘርፉ ካሉ አዳዲስ አሠራሮችና የቴክኖሎጂ እድገቶች አኳያ ከዘመኑ ጋር በተጣጣመ መልኩ መከለሱ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ባለፉት ዓመታት የአዲስ ሕግ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል። ብዙ ምክክር ተደርጎበት የጸደቀው የሕግ መድብል አዳዲስ አሠራሮችን የሚያስተዋውቅ፤ የወንጀል ምርመራ፣ ክስና ማስረጃ ሥርዓቱን ወደአዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው ሲልም አስገንዝቧል ጽሕፈት ቤቱ።
ባሳለፍነው ሳምንት
Mar 28, 2026 546
በዮሐንስ ደርበው ከመጋቢት 13 እስከ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል • ‎የ ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን እና የሰው ልጅ ታሪክ በጀመረበት ምድር የተገነባውን ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅት ሎጁ የዛሬ 50 እና 60 ዓመት መሠራት የነበረበት ቢሆንም፤ አሁን ስለዘገየን አንቆጭም ማለታቸው ይታወሳል። ይህን ስለሠራንም አንረካም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሩጫችን ገና ብዙ እንደሆነ፣ አፋር ገና እንዳልተነካ አስበን ይህን ጅማሮ ይበልጥ በማላቅ ለማስቀጠል እንተጋለን ሲሉም ተናግረዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከቃና ቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በኢትዮጵያ ከተሞች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነም ገለጻ አድርገዋል። እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸውን ፋይዳም አንስተዋል። • ኢትዮጵያ በማላቦው ጉባዔ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ ወደ ማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ ያቀኑት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ማላቦ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ማኑዌል ኡሳ ኡዙዌን ጨምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጉባዔው ከመጋቢት 18 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ ሲሆን እስከ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቀጥላል። • የልማት ሥራዎች ጉብኝት በባሕር ዳር እና ጎንደር ከተሞች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የባሕር ዳር ከተማን የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያጎሉና ግንባታቸው እየተፋጠኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የመንገድ መሠረተ-ልማት እና የአየር መንገድ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለኢኮኖሚ ዕድገታችን የጎላ ፋይዳ ይኖራቸዋል ሲሉም በወቅቱ ገልጸዋል። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጎንደርን የውኃ ጥም ይቆርጣል፤ የገበሬውን መሬት ያጠጣል፤ የአካባቢውን ምኅዳር ይለውጣል የተባለው የመገጭ የመጠጥ ውኃ ግድብ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተዋል። በዚሁ ወቅት የሀገር ሀብት ፈስሶባቸው መክነው እና ባክነው የቀሩ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ከሞት እያስነሡ ማፋጠን የዚህ መንግሥት ልዩ መለያው ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም የመገጭ ግድብ ምስክር መሆኑን ጠቅሰዋል። እንዲሁም በጎንደር ከተማ አሥተዳደር ሳይና ሳቢያ የገጠር ቀበሌ የተገነቡ የገጠር ኮሪደር ሞዴል ቤቶችን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት መርቀዋል። በዚሁ ወቅትም በአንድ ወር የግንባታ ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀው ይህ ሞዴል መንደር በአካባቢው ለረጅም ዓመታት የቆየውን የጤና ጣቢያ፣ የመብራትና የውኃ አገልግሎት ጥያቄ በተግባር መልሷል ብለዋል። በሀገራችን ከተማው ብቻ ሳይሆን ገጠሩም እኩል እየተዋበ፣ በልማት እየተገነባና በዕድገት ፍኖት ላይ በጽኑ መሠረት እየተራመደ ይገኛልም ነው ያሉት። ይህ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የማሸጋገር ትልቁ ማሳያችን ነው ሲሉም ገልጸዋል። • "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ በአዲስ አበባ 4ኛው "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረም ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም፤ የምንፈልገው ድጋፍን ሳይሆን አጋርነትን ነው፤ እርዳታን ሳይሆን ኢንቨስትመንትን ነው! ለባለ ሀብቶች ምቹ፣ ግልጽና ተራማጅ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ አዘጋጅተናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ካፒታል፣ ለችሎታ እና ለዕድል በሯን ወለል አድርጋ መክፈቷንም አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ አሁን በፍጥነት ወደ ከፍታ እየገሠገሠች ባለችበት በዚህ ታሪካዊ የዕድገት ጉዞ፤ ለዓለም አቀፍና ለሀገር ውስጥ ባለ ሀብቶች ኢትዮጵያ ለእናንተ ዝግጁ የሆነ፣ በዕድሎችና በስኬቶች የተሞላ ታላቅ የኢንቨስትመንት መሶብ አላት፤ ኑ አብረን እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል! • የትግራይ ክልል አጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት የትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደት ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) በሰጡት መግለጫም፤ ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን ለመጀመርና ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል። በዚህም ከክልሉ ጊዜያዊ አሥተዳደር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀሌ እና በአዲስ አበባ ከ22 ጊዜ በላይ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ጥረቶች ውስጥ ሂደቱን በክልሉ ለማካሄድ የሚያስችሉ አስቻይ ሁኔታዎች ባለመፈጠራቸው፤ የአጀንዳ ማሰባሰብና የተወካዮች ምርጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ እንዲከናወን መወሰኑንም አስረድተዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3867
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2628
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8419
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6907
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60836
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54822
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35332
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32947
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27959
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 27189
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26687
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26274
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60836
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54822
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35332
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32947
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 428
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ
Apr 12, 2026 920
በኅብረትና ጽናት የሚቀረጽ ብርሃን፤ የኢትዮጵያ ትንሣኤ በቀበኔሳ ገቢሳ ትንሣኤ ለሰው ልጅ ተስፋን፣ ዘለዓለማዊ ሕይወትን እና ከኃጢአት ነፃ መውጣትን የሚያበስር ኃይማኖታዊ በዓል ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ በመነሳቱ የሰው ልጅ የዘለዓለም የሕይወት አክሊልን ተስፋ ያደረገበት፣ የእግዚአብሔር ፍቅር የተገለጠበት እንዲሁም የሰው ልጅ ከዘለዓለም ሞትና ከኃጢአት ባርነት ነፃ የወጣበት የድኅነት፣ የፍቅር፣ የጽናትና የተስፋ ብርሃን ብስራት ነው፡፡ የትንሣኤ በዓል ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የመነሳቱ ታላቅ ምሥጢር የሚታሰብበት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንስ የሰው ልጅ ከውርደት ወደ ክብር፣ ከኃጢያት ባርነት ወደ ድኅነት እንዲሁም ከጉስቁልና ወደ ብሩህ ተስፋ የተሸጋገረበት የድል አዋጅ ነው። በዕለቱም በሞት ላይ ሕይወት፣ በሐዘን ላይ ደስታ፣ በቂም ላይ ይቅርታ ተበስሮበታል። ከበዓላት ሁሉ የላቀ የነጻነት ተምሳሌት ነው ትንሣኤ። 👉የትንሣኤ ሕያው አስተምሮ በዕለት ተዕለት ሕይወት ትንሣኤ ሲከበር ከሥርዓተ አምልኮ ባለፈ፣ በዓሉ የሚሰጠውን ታላቅ አስተምሮ ማጤን ይገባል። ትንሣኤ በየቀኑ ካለንበት ድካምና ውድቀት በአዲስ መንፈስ የመነሳት አቅም ነው። በዓሉ የሚያስተምረንን የጽናት፣ የተስፋና የአብሮነት ዕሴት በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ መኖር ያስፈልጋል። ለዚህም የተቸገሩን መርዳት፣ የታመሙትን መጠየቅና የተጣሉትን ማስታረቅ የበዓሉን ትርጉም እውነተኛ ያደርገዋል። 👉የኢትዮጵያ ትንሣኤ፤ በፈተና የጸና ብርሃን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዓሉን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት፤ "የዘንድሮውን የትንሣኤ በዓል የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በፈታኝ የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ሆና እያለች ነው። መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችንም እሾህ የበዛበት ሊሆን ይችላል። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ፣ በጨለማ ወጥመድ ሊያሥሩን የሚሞክሩ መሰናክሎች ቢበዙም፣ እምነታችን ግን ከሕማማት በኋላ ትንሣኤ እንደሚመጣ ነው" ብለዋል፡፡ "ኢትዮጵያ ዛሬም ትንሳኤዋን እያየች ነው። መቃብሯ ተከፍቷል፤ ማኅተሙም ተሰብሯል። የትንሣኤውን ዜና ሊያደበዝዙ የሚሞክሩ የውሸት ወሬዎችና ተስፋ አስቆራጭ ትረካዎች የሀገራችንን የብርሃን ጉዞ ሊገቱት አይችሉም። ትንሳኤው እውነት ነው፤ ብርሃኑም የማይቀለበስ ሀቅ ሆኗል" ሲሉም አረጋግጠዋል፡፡ 👉ዴሞክራሲ እና ብሔራዊ ምክክር፤ የተስፋ ምዕራፎች የኢትዮጵያ ትንሣኤ አንዱ መገለጫ ዴሞክራሲን የመገንባት ጽናት ነው። ትንሣኤ ያለ ሕማማት እንደማይገኝ ሁሉ ዴሞክራሲ ያለ ፈተና በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ዴሞክራሲ የሚገነባው በጽናት እንጂ በፍርሃት አይደለም። ዴሞክራሲን እየገነባን በትዕግሥትና በቆራጥነት ወደ ተስፋዋ ምድር እንደርሳለን። አሁን ያለው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጦርነት፣ የኢኮኖሚ ቀውስና ማህበራዊ አለመረጋጋት የትንሳኤን ትምህርት ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊ ያደርገዋል፡፡ ችግሮችን በብቸኝነት የምንወጣበት ጊዜ አብቅቷል። ዛሬ እንደህዝብ የሚያስፈልገን ከ"እኔ" ወደ "እኛ" መሸጋገር፣ የግል ፍላጎትን ለጋራ ስኬት መስዋዕት ማድረግ ግድ የሚልበት ወቅት ላይ ነን። የአንድነት ጉዟችንን በማጠናከር ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ጫናዎችን ለመቋቋም በጋራ መቆም ይገባናል። የተቸገሩትን በመርዳት፣ የታመሙትን በመጠየቅና የተጣሉትን በማስታረቅ የተግባር አብሮነትን በማሳየት የበዓሉን እውነተኛ ትርጉም መግለጥ ይገባል፡፡ 👉ምርጫ፤ ከኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበትና ተስፋ የታደሰበት ዕለት ነው። እኛም በምርጫ ካርዳችን የሃሳብ ልዩነትን በዴሞክራሲያዊ አንድነት ድል በማድረግ የኢትዮጵያን የብልፅግና ትንሳኤ እናረጋግጣለን። በትንሣኤ በዓል የምንማረው ይቅርታና ጽናትም ለምርጫችን ስኬት አቅም ይሆናል። በኅብረት የምንሰጠው ድምፅም የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ የመቅረጽ ኃይል በእጃችን መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው "ምርጫ የኢትዮጵያን ትንሣኤ ማብሰሪያዎች አንዱ ምዕራፍ ነው። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም። በዓለም ላይ በደልዳላ መንገድ ተጉዞ ዴሞክራሲን የገነባ ሀገር የለም። ዴሞክራሲና ብልፅግና ያለ ጽናት አይሳኩም። ከእኛ በፊት ዐመጻውን በትዕግሥት የመከቱ ተሻግረዋል፤ ሑካታውን በጽናት ያለፉ አሳክተዋል። ብንመኝም ፈተናውን አናስቀርም፤ መጽናት ግን እንችላለን። ከድኅነት መውጫው ብርታታችን፣ ወደ ዴሞክራሲ መድረሻችው ትዕግሥታችን እንደሆነ አምነን ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በሙሉ ልባችን እንትጋ!!" ብለዋል። 👉የወደፊት እጣ ፈንታችን በእጃችን ከፊታችን የሚጠብቁን ሀገራዊ ምክክርና የ2018 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የወደፊት መጻኢ ዕድል የሚወስኑ ታላላቅ ሁነቶች ናቸው። እነዚህ ሂደቶች ስኬታማ የሚሆኑት እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን ሲወጣ ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በልባችን ውስጥ ይቅርታና አብሮነት ሲነግስ ብቻ ግቡን ይመታል። ትንሣኤ ሞት ድል የተነሳበት እንደሆነው ሁሉ፣ በምክክሩም ጥልን፣ ጥርጣሬን፣ ያለመግባባት መንፈስን ድል መንሳት ይገባል፤ ቅንነት፣ ተስፋና መተሳሰብ ለምክክሩ ስኬት የመተማመኛ ቁልፎች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ 2018 ዓ.ም ደግሞ የዜጎች ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ ማሳያ አንጓ ነው፤ የዜጎች ነፃ ተሳትፎ መብታቸውን የሚያስከብሩበት ፍላጎታቸውን የሚያረጋግጡበት ማረጋገጫ ማህተም ጭምር፡፡ ዜጎች የመምረጥና የመመረጥ መብታቸውን የሚያስከብሩበት፤ የሌላውን ሃሳብ አክብረው የራሳቸውን የሚያስከብሩበት ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በጋራ የሚቆሙበት መድረክ ነው፡፡ ትንሣኤ የድልና የነጻነት በዓል ነው። ይህንን ታላቅ ዕለት ስናከብር ያለፈውን ቁስል ሽረን፣ ለነገ ተስፋ ሰንቀን መሆን አለበት። እርስ በእርስ በመደጋገፍ፣ ችግሮችን በንግግር በመፍታት ለሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ስኬታማነት የድርሻችንን መወጣት ይገባናል። የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ እንቁም! መልካም የትንሳኤ በዓል!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም