ኢዜአ - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መስተጋብር እሴቶች እንዲጎለብቱ መሥራት ይገባናል-ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ
Dec 1, 2023 2
ሐረር፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያውያን የአብሮነትና የአዎንታዊ መስተጋብር እሴቶች እንዲጎለብቱ መሥራት ይገባናል ሲሉ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ አስገነዘቡ። በሐረር ከተማ 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በድምቀት ተከብሯል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት “የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ኢትዮጵያ የብዝሃነት አገር መሆኗን በተጨባጭ የሚያሳይ ነው።'' በዓሉ የተለያየ ቋንቋ፣ ባህልና ታሪክ ያላቸው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች አንድነታቸውን ያጠናከሩበት መሆኑንም አመልክተዋል። በተጨማሪም ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ እያገዘ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ያስታወቁት። አቶ ኦርዲን እንዳሉት የክልሉ መገለጫ የሆኑ የአንድነት፣ የአብሮነትና የአዎንታዊ መስተጋብር እሴቶች እንዲጎለብቱ ቀጣይነት ያላቸው ሥራዎች ማከናወን ይገባል። "የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በማህበራዊ መስተጋብሮቻችን ያለንን አንድነት በማጠናከር ለሀገር ብልጽግና መሥራት ይገባናል" ሲሉም ተናግረዋል። በክልሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማቃለልና ለሕዝብ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል። በተጨማሪም በተቋማት የሚታዩ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ በዓሉ ያስገኘውን ትሩፋት ማስቀጠል ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል። የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም በበኩላቸው የዘንድሮ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል “ብዝሃነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት!'' በሚል ቃል በክልሉ በልማትና በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር መቆየቱን አስታውሰዋል። ኅዳር 29 ለኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እውቅና የሰጠ ሕገ መንግሥት የፀደቀበት ዕለት መሆኑን ያስታወሱት አፈ ጉባዔው፤ በዓሉ የኢትዮጵያውያንን አንድነት ያጠናከረና እርስ በእርስ ያስተሳሰረ ነው ብለዋል፡፡ በዓሉ የህዝቦች የእኩልነት መብት በሕገ መንግሥት የተረጋገጠበት መሆኑን አስታውሰው፣ የክልሉ ሕዝብ በጅግጅጋ ከተማ በሚከበረው በዓል ላይ የሚታደሙ እንግዶችን ተቀብሎ እንዲያስተናገድም አስገንዝበዋል። በበዓሉ የተሳተፉት አቶ ቶፊቅ መሐመድና ወይዘሮ ነቢላ መሐመድ በበኩላቸው አብሮነትንና አንድነትን በማጠናከር በክልሉ የተጀመሩ የሰላምና የልማት ሥራዎችን ለማስቀጠል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የክልሉን ሕዝብ የልማት ጥያቄዎችን በተሻለ ለመመለስና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራም ጠይቀዋል። አገራዊ አንድነት የሰፈነባት የተሻለች ኢትዮጵያን መፍጠር በሚያስችል መልኩ በዓሉን ማክበር እንደሚገባም ተናግረዋል። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል።
የቻይና ኮንግረስ ፓርቲ አባላት ገላን የሚገኘውን ኤ ኤም ጂ ቡና ላኪ ድርጅትን ጎበኙ
Dec 1, 2023 22
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፣- የቻይና ኮንግረስ ፓርቲ የግብርናና የገጠር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ገላን የሚገኘውን ኤ ኤም ጂ ቡና ላኪ ድርጅት ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ሎሚ በዶና ሌሎች የምክር ቤት አባላትም ተገኝተዋል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ እንዳሉት፣ ኢትዮጵያ የተለያዩ ተወዳጅ ጣዕም ያላቸው ቡና በስፋት በማምረት ለተለያዩ አገራት በመላክ ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል። የምትልከው ቡና በጥራትም ሆነ በማምረት አቅም እየጨመረ ይገኛል ብለዋል። ኢትዮጵያ ቡና ከምትልክባቸው አገራት መካከል ቻይና ተጠቃሽ መሆኗን አስረድተው፤ የቻይና ባለሃብቶች በዘርፉ በስፋት ቢሰማሩ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አብራርተዋል። በቻይና ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ የግብርናና የገጠር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዱ ጂሃኦ በበኩላቸው በቻይና ገበያ የኢትዮጵያ ቡና እየታወቀ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ከጉብኝቱም የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በቡና ዘርፍ በስፋት መሰማራት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩን መገንዘባቸውን ገልጸዋል። የቻይና ባለሀብቶች በቡና ማቀነባበሪያ ዘርፍ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል።
በሥራ ላይ የቆየውን የሙስና መከላከል ስትራቴጂ በመከለስ ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው - የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
Dec 1, 2023 21
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፦ በሥራ ላይ የቆየውን የሙስና መከላከል ስትራቴጂ በመከለስ ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ። "ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው፤ በኅብረት እንታገል" በሚል መሪ ኃሳብ 20ኛው አገር አቀፍ የፍትህ ተቋማት የፀረ-ሙስና ቀን የምክክር መድረክ ተካሂዷል። የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ጊዜ፤ ሙስና አገርን እድገት በመፈተን የፍትሕ ተቋማትን ተዓማኒነት አደጋ ላይ የሚጥል የሥነ-ምግባር ጉድለት ነው ብለዋል። ፍርድ ቤቶች ፍትሕ ሰጪ ተቋማት በመሆናቸው በዳኝነት ሂደት ሕዝብና መንግሥት የጣለባቸውን አደራ በፍጹም ታማኝነት በመወጣት ለሙስና ትግሉ አዎንታዊ ሚና መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። የፍትሕ ተቋማት በሙስና ወንጀል ተጋላጭነት የሚፈተኑ በመሆናቸው ጫናውን በመቋቋም አገራቸውንና ሕዝባቸውን በታማኝነት በማገልገል ተጠያቂነት የማስፈን አገራዊ አደራ እንዳለባቸው አስገንዝዋል። የሙስና ወንጀል በፍትሕ ተቋማት ላይ ጥያቄ የሚያስነሳ ከሆነ የፍርድ ቤቶችን ተዓማኒነት በማጉደል ዜጎች በፍትሕ ተቋማቱ ላይ እምነት እንዲያጡ ያደርጋል ብለዋል። ሙስናን መከላከል ካልተቻለ እድገትና ኢንቨስትመንት እንዲገታ በማድረግ ውጤታማነትና ፈጠራን በማዳከም በአገርን ህልውና ውስጥ እንደሚከት ገልጸዋል። በዚሁ መነሻነትም ፍርድ ቤቶች የሙስና ተጋላጭነትን በመቀነስና ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። ለዚህም በሥራ ላይ የቆየውን የሙስና መከላከል ስትራቴጂ በመከለስ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል የክለሳ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። የፌዴራል የሥነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ምክትል ኮሚሽነር እሸቴ አስፋው፤ ሙስናን ለመከላከል የሃብት ምዝገባ፣ የተጋላጭነት ጥናት፣ የሥነ-ምግባር ግንባታና ግንዛቤ ፈጠራ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የፍትሕ ተቋማት የሙስና ተጋላጭነት አመላካች የጥናት ውጤት መካሄዱን ጠቅሰው፤ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተጋላጭነት ጥናት ውጤቱን ተግባራዊ ለማድረግ የወሰደውን ተነሳሽነት አድንቀዋል። የመሬት ዘርፍ፣ የካሳ ክፍያ፣ የመንግስት ግዥ፣ ሕገ-ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ፣ የመንግስት አገልግሎት ግንባር ቀደም የሙስና ተጋላጭ ዘርፎች መሆናቸው አመላክተዋል። የሙስና ወንጀል ለመከላከል ከፍትሕና ተጋላጭነት ከሚስተዋልባቸው ተቋማት ጋር በመተባበር ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በመድረኩም አገራዊ የሙስና ተጋላጭነትን ዓለም አቀፋዊ ተሞክሮን የሚያመላክቱና የፍትሕ ተቋማት የሙስና ተጋላጭነትን የሚያሳዩ የመነሻ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ምክክር ተደርጎባቸዋል።
በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሥርጭት በስፋት በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የቅድመ መከላከል ስራ በትኩረት ይሰራል
Dec 1, 2023 35
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሥርጭት በስፋት በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የቅድመ መከላከል ስራው በትኩረት እንደሚሰራ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የዓለም ኤድስ ቀን "የማህበረሰብ መሪነት የኤች አይ ቪ ቫይረስ መከላከል" በሚል መሪ ሀሳብ በአለም አቀፍ ደረጃ ለ36ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ35ኛ ጊዜ ተከብሯል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የዓለም ኤድስ ቀን ሲከበር ህብረተሰቡ የኤች አይ ቪ ቫይረስ በመከላከል የመሪነት ሚናውን እንዲወጣ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ሚኒስቴሩ ለቫይረሱ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ አብራርተዋል፡፡ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭት ምጣኔን በመከላከል ረገድ መንግስትና ማህበረሰቡ ባደረጉት ጥረት እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር በ2010 ከነበረበት 1 ነጥብ 26 በመቶ በ2022 ወደ 0 ነጥብ 91 በመቶ መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ቫይረሱ በደማቸው ይገኛል ተብሎ ከሚገመቱ ሰዎች መካከል 84 በመቶ የሚሆኑት ተመርምረው ራሳቸውን እንዲያውቁና ከነዚህም ውስጥ 98 በመቶው የጸረ-የኤች አይ ቪ መድሃኒት እንዲጠቀሙ ማድረግ ተችሏል። ነገር ግን አሁንም የቫይረሱ ስርጭት በስፋት የሚስተዋልባቸው አካባቢዎች በመኖራቸው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ስርጭቱን ለመግታት እንደሚሰራ ዶክተር ሊያ ተናግረዋል። በተለይ የመገናኛ ብዙሃን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም አጀንዳ በማድረግ በትኩረት መስራት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። በአለም አቀፍ ደረጃ ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱን ገልጸው፤ ችግሩን ለማጥፋት ግን አፍላ ሴት ወጣቶች ላይ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በጤና ሚኒስቴር የኤች አይቪ መከላከል እና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈጻሚ ፍቃዱ ያዴታ በበኩላቸው፤ የዓለም አገራት በ2030 ኤች አይ ቪ ኤድስ ለማኅበረሰቡ ሥጋት ወደ ማይሆንበት ደረጃ ለማድረስ ጥረት በማረግ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የተ.መ.ድ የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከል መርሃ ግብር (ዩ ኤን ኤድስ) ዳይሬክተር ፍራኮዝ ናዪሺሚ በበኩላቸው በኢትዮጵያ ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ባለፉት ዓመታት አመርቂ ስራዎች እንደተሰሩ ገልጸዋል። በተለይ የማህበረሰብ አቀፍ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ስራው የቫይረሱ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መጥቷል ብለዋል። በመድረኩ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ በዘርፉ የሚሰሩ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ አምባሳደሮች፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በአማራ ክልል ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የመደገፍና የማበረታታት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 1, 2023 39
ጎንደር፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የመደገፍና የማበረታታት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ዶክተር አህመዲን መሃመድ ገለጹ። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር አህመዲን መሃመድ በጎንደር ከተማ የሚገኘውን አባይ ጋርመንት ፋብሪካ የምርት እንቅስቃሴን ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡ ዶክተር አህመዲን በዚሁ ጊዜ በክልል ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍና በማበረታታት በኩል በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የጨርቃ ጨርቃና አልባሳት አምራች ኢንዱስትሪዎች ከውጪ የሚገቡ የአልባሳት ምርቶችን በማስቀረት ሰፊ ሚና እንዳላቸው ጠቁመው፤ የግብዓት አቅርቦትና የገበያ ትስስር በመፍጠር ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ''የአባይ ጋርመንት ፋብሪካም ከውጪ የሚገቡ አልባሳትን በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት ሰፊ አቅም እንዳለው መገንዘብ ችለናል'' ብለዋል ዶክተር አህመዲን፡፡ ፋብሪካው በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች የተደራጀና በገበያ ተፈላጊ የሆኑ ጥራትና ተወዳዳሪነት ያላቸው አልባሳትን የማምረት አቅም አሟጦ እንዲጠቀም ድጋፍ ይደረጋልም ብለዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ በበኩላቸው፤ የፋብሪካው በአካባቢው መቋቋም ለስራ አጥ ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር የጎላ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች መጠናከርና መበራከት ከመሬት አቅርቦት ጀምሮ የተለያዩ የማበረታቻ ስርዓቶችን በመዘርጋት እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የፋብሪካው ዋና ስራ አስኪያጅ ማናየሽ ተሰማ እንደተናገሩት፤ ፋብሪካው ጂንስ ሱሪዎችንና ቲሸርቶችን ጨምሮ የተለያዩ አልባሳትን በማምረት ለሀገር ውስጥ ገበያ እያቀረበ ነው፡፡ ፋብሪካው ባለፈው ዓመት ለሀገር ውስጥ ገበያ ካቀረበው የአልባሳት ምርት ከአንድ ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጪ ምንዛሬ ማዳኑን ጠቁመው፤ ዘንድሮም በተመሳሳይ ዕቅዱን ለማሳካት በምርት ስራ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ ዘመኑ የደረሰባቸውን የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች በመጠቀም በተለያዩ ዲዛይኖችና የጥራት ደረጃዎች ልዩ ልዩ የአልባሳት ምርቶችን ለሀገር ውስጥ ገበያ እያቀረበ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ፋብሪካው በአሁኑ ወቅት 800 ለሚደርሱ ሰራተኞች ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው፤ በሙሉ አቅሙ ወደ ማምረት ሲሸጋገር ለ3 ሺህ ያህል ሰራተኞች የስራ እድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡ በጎንደር ከተማ የሚገኘው በአባይ ኢንዱስትሪ ልማት አክሲዮን ማህበር የአባይ ጋርመንት ፋብሪካ በ2012 ዓ.ም በ450 ሚሊዮን ብር ወጪ በክልሉ መንግስትና በባለሃብቶች ትብብር የተቋቋመ ነው።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መስተጋብር እሴቶች እንዲጎለብቱ መሥራት ይገባናል-ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ
Dec 1, 2023 2
ሐረር፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያውያን የአብሮነትና የአዎንታዊ መስተጋብር እሴቶች እንዲጎለብቱ መሥራት ይገባናል ሲሉ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ አስገነዘቡ። በሐረር ከተማ 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በድምቀት ተከብሯል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት “የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ኢትዮጵያ የብዝሃነት አገር መሆኗን በተጨባጭ የሚያሳይ ነው።'' በዓሉ የተለያየ ቋንቋ፣ ባህልና ታሪክ ያላቸው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች አንድነታቸውን ያጠናከሩበት መሆኑንም አመልክተዋል። በተጨማሪም ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ እያገዘ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ያስታወቁት። አቶ ኦርዲን እንዳሉት የክልሉ መገለጫ የሆኑ የአንድነት፣ የአብሮነትና የአዎንታዊ መስተጋብር እሴቶች እንዲጎለብቱ ቀጣይነት ያላቸው ሥራዎች ማከናወን ይገባል። "የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በማህበራዊ መስተጋብሮቻችን ያለንን አንድነት በማጠናከር ለሀገር ብልጽግና መሥራት ይገባናል" ሲሉም ተናግረዋል። በክልሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማቃለልና ለሕዝብ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል። በተጨማሪም በተቋማት የሚታዩ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ በዓሉ ያስገኘውን ትሩፋት ማስቀጠል ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል። የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም በበኩላቸው የዘንድሮ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል “ብዝሃነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት!'' በሚል ቃል በክልሉ በልማትና በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር መቆየቱን አስታውሰዋል። ኅዳር 29 ለኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እውቅና የሰጠ ሕገ መንግሥት የፀደቀበት ዕለት መሆኑን ያስታወሱት አፈ ጉባዔው፤ በዓሉ የኢትዮጵያውያንን አንድነት ያጠናከረና እርስ በእርስ ያስተሳሰረ ነው ብለዋል፡፡ በዓሉ የህዝቦች የእኩልነት መብት በሕገ መንግሥት የተረጋገጠበት መሆኑን አስታውሰው፣ የክልሉ ሕዝብ በጅግጅጋ ከተማ በሚከበረው በዓል ላይ የሚታደሙ እንግዶችን ተቀብሎ እንዲያስተናገድም አስገንዝበዋል። በበዓሉ የተሳተፉት አቶ ቶፊቅ መሐመድና ወይዘሮ ነቢላ መሐመድ በበኩላቸው አብሮነትንና አንድነትን በማጠናከር በክልሉ የተጀመሩ የሰላምና የልማት ሥራዎችን ለማስቀጠል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የክልሉን ሕዝብ የልማት ጥያቄዎችን በተሻለ ለመመለስና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራም ጠይቀዋል። አገራዊ አንድነት የሰፈነባት የተሻለች ኢትዮጵያን መፍጠር በሚያስችል መልኩ በዓሉን ማክበር እንደሚገባም ተናግረዋል። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል።
የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነድ እያዘጋጀ ነው
Dec 1, 2023 34
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚያደርገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ለማስቻል የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነድ እያዘጋጀ ነው። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ያዘጋጀውን ረቂቅ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነድ በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል። ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚሰሩ ሥራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ረቂቅ ሰነድ ተዘጋጅቷል። ይህም ወቅታዊ፣ ግልጽና ቀልጣፋ መረጃዎችን የመለዋወጫ ምህዳር ለማስፋት ያስችላል ነው ያሉት። የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነዱ በተለይም ኮሚሽኑ ለተለያዩ ባለድርሻና አጋር አካላቶች የሚያስተላልፋቸውን መረጃዎች በምን መልኩና ለማን ምን አይነት መረጃ መቅረብ አለበት የሚለውን ለማመላከት ወሳኝ ነው ብለዋል። በቀጣይ ኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነዱን ከዘርፉ ተዋናዮች የሚሰጡት ገንቢ ሃሳቦች በማዳበር ሥራ ላይ እንደሚውል ጠቁመዋል። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሻንቆ ደለለኝ በበኩላቸው የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነዱ የቀድሞ ተዋጊዎች ወደ ማኅበረሰቡ ሲቀላቀሉ በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆኑ የማኅበረሰቡን ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሰፊ እድል እንዳለው ገልጸዋል። የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ትልቅ ሃብትን የሚጠይቅ በመሆኑ አጋር አካላቶች በዚህ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማጠናከር የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነዱ ጠቀሜታ እንደሚኖረውም አመላክተዋል።
ወጣቶች በግንባር ቀደምነት ለሰላም ዘብ ሊቆሙ ይገባል
Dec 1, 2023 37
ባህር ዳር፤ ህዳር 21 /2016 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላም ለማስፈን እየተደረገ ባለው የተቀናጀ ጥረት ወጣቶች በግንባር ቀደምትነት ለሰላም ዘብ ሊቆሙ እንደሚገባ የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ጋሻው ተቀባ ገለጹ። “ድንበር ተሻጋሪ የወጣቶች እንቅስቃሴ ለፓን አፍሪካኒዝም” በሚል መሪ ሃሳብ 17ኛ የአፍሪካ ወጣቶች ቀን በባህር ዳር ከተማ ዛሬ ተከብሯል። የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ጋሻው ተቀባ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ለአንድ አገር ሁለንተናዊ እድገት ሰላም ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ባጋጠመው የጸጥታ ችግር በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩን አውስተው፤ ለዘላቂ መፍትሄው ወጣቶች በተደራጀ አግባብ መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። በተለይም አስተማማኝ ጸጥታ ለማስፈን መንግስት በተቀናጀ አግባብ እያደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ ወጣቶች በግንባር ቀደምትነት ለሰላም ዘብ መቆም እንደሚገባቸው አመልክተዋል። ሃገር የምትገነባው በወጣቶች የበሰለ ሃሳብና ተግባር እንደሆነ ጠቅሰው፤ አሁን ላይ በክልሉ እየተስተዋለ ያለው ችግር እንዲፈታ በባለቤትነት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሰላምና ደህንነት ትምህርት ክፍል መምህርና ጽሁፍ አቅራቢ ዶክተር ፍቅርተ አዱኛ እንደገለጹት፤ ወጣቶችን ወደ አመራርነት በማምጣት የሰላም ተዋናይ እንዲሆኑ መስራት ያስፈልጋል። ወጣቶች የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ባህል በማዳበር መንቀሳቀስ እንዳለባቸውም አብራርተዋል። እንደ አማራ ክልል ወጣት በተለይም በዚህ ወቅት ሰለ ሰላም በስፋት መስራት የሚጠይቅበት ወቅት መሆኑንም ገልጿል። ሰላምን ለማረጋገጥ መንግስት ከሚያከናውናቸው ተግባራት ጎን ለጎን የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ እንደሆነ የገለጸችው ደግሞ ወጣት አኒሻ ወርቁ ናት። ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን ወጣቶች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ጠቅሳ፤ ወጣቶች የሚያነሷቸውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ መፍታት እንዳለበትም ጠቁማለች። በባህርዳር በተከበረው የአፍሪካ ወጣቶች ቀን መረሃ ግብር ላይ የከተማ አስተዳደሩ የአመራር አባላትና የከተማው ወጣቶች ተሳታፊ ሆነዋል።
በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን በአንድ ጥላ በማሰባሰብ ባህልና እሴቶቻቸው ጎልቶ እንዲወጣ አድርጓል-የሰመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች
Dec 1, 2023 37
ሰመራ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፦በዓሉ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን በአንድ ጥላ ስር ከማሰባሰብ ባለፈ ባህልና እሴቶቻቸው ጎልቶ እንዲወጣ ያደረገ ነው ሲሉ በአፋር ክልል የሰመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በዓሉ እርስ በርስ ለመተዋወቅ፣ አንድነትን ለማጠናከር እና እኩልነትን በተግባር ለማረጋገጥ የቻሉበት መሆኑንም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። 18ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በአፋር ከልል ደረጃ ሲከበር የተሳተፉ የከተማው ነዋሪዎች እንዳሉት፣ ባለፉት ዓመታት የተከበረው በዓል የሀገሪቱ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እርስ በርስ እንዲተዋወቁ አድርጓል። አንዱ የሌላውን ባህል እንዲያውቅና እንዲያከብር እንዲሁም ተደብቀው የነበሩ ቱባ ባህሎች አደባባይ እንዲወጡ ማድረጉን ገልጸዋል። በተጨማሪም እኩልነትን በተግባር ከማሳየት ባለፈ፤ የአገር ባለቤትነት ስሜት በብሔር ብሔረሰቦች መካከል መሠረት እንዲይዝ እያደረገ መሆኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የሠመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪ አቶ ኑሩ ደበሌ በየዓመቱ በሚከበረው በዓል ላይ እንደሚሳተፉ ገልጸው፣ በዓሉ የእርስ በርስ ትብብርን ለማጠናከር ይገኛል ብለዋል። ''ኢትዮጵያውያን እጅ ለእጅ ተያይዘን ለአገር ልማት በአብሮነት መጓዝ ይገባናል'' ያሉት አቶ ኑሩ፣ በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦች በአንድ ጥላ አንዲሰባሰቡ አስችሏል ብለዋል። የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ባህልና እሴቶች ቀደም ባሉ ሥርአቶች ተገቢ ትኩረት ሳይሰጣቸው መቆየታቸውን የገለጹት ደግሞ አቶ ሰይድ ሙክተባ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። ቀኑ መከበሩ ህዝቦች ባህልና አሴታቸውን እንዲያጎለብቱ፣ እኩልነትን በተግባር እንዲያረጋግጡና አብሮነትን እንዲያጠናክሩ አስችሏል ሲሉም ገልጸዋል። የማይታወቁ ብሔረሰቦች ባህልና ቋንቋቸው እንዲታወቅ ማድረጉንም ጠቁመዋል። የብሔር ብሔረሰቦችን ቱባ ባህል፣ ቋንቋና እሴቶች ለማጎልበት በዓሉ ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የገለጹት ደግሞ አቶ ሁሴን መሐመድ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። እንደ እሳቸው ገለጻ በዓሉ በየዓመቱ መከበሩ አንዱ ብሔር ከሌላው ጋር እንዲተዋወቅ፣ ተከባብሮ አንዲኖርና በአገራዊ ጉዳይ አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ እያደረገ ነው። የሠመራ ከተማ ነዋሪ ወጣት አሊ ሰለለ በበኩሉ በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በአብሮነት ደምቀው የሚታዩበት መሆኑን ገልጿል። በበዓሉ ብሔር/ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቋንቋቸውን፣ ማንነታቸው እና ቱባ ባህላቸውን በአብሮነት ሲያሳዩ የኢትዮጵያዊያን የተለያዩ መልኮች ይንጸባረቃሉ ያለው ወጣት አሊ፣ በዓሉ አብሮነትን ስለሚያጎለብት መጠናከር አለበት ብሏል። ዘንድሮ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ህዳር 29 ቀን 2016 ዓ.ም "ብዝሃነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ እንደሚከበር ታውቋል።
ኢትዮጵያና እስራኤል የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
Dec 1, 2023 58
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና እስራኤል የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር መስማማታቸው ተገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በውይይታቸው አምባሳደር ምስጋኑ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቆየ የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ተከታታይ የሀሳብ ልውውጥ ማድረግ እንደሚያስፈልግ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ግንኙነቱን ለማጎልበትም በቀጣይ የሁለትዮሽ አሰራሮችን መፈተሽ እና የፖለቲካ ምክክር ማድረግ እንደሚገባም አምባሳደር ምስጋኑ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር መመስረት ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የጎላ ጠቀሜታ አለው - አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ
Dec 1, 2023 71
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር መመስረት ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገለጹ። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያየ ጊዜ አገራቸውን ለረጅም ጊዜ በልዩ ልዩ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ የነበሩ የቀድሞ እና አንጋፋ አምባሳደሮችን፣ ዲፕሎማቶችንና በአሁኑ ወቅት እያገለገሉ ያሉ የመሥሪያ ቤቱ ባለሙያዎችን ያካተተ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር ተመስርቷል። በማኀበሩ ምስረታ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ የአገራቸውን ብሔራዊ ጥቅም እና ክብር እንዲጠበቅ ያደረጉ አንጋፋ ዲፕሎማቶችን እና የአሁኑን ትውልድ ባለሙያዎች የሚያሰባስበው ማኀበር መመስረቱ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል። ማኀበሩ በውጭ ግንኙነት ሥራ ውስጥ በጥናት እና ምርምር፣ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን በማሳየት እንዲሁም ወጣቶችን በማሰልጠን የእውቀት ሽግግር በማድረግ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ አምባሳደሩ መናገራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል። በማኀበሩ ምሥረታ ላይ የተገኙ አንጋፋ ዲፕሎማቶች የሙያ ማኀበር መመስረቱ የዲፕሎማሲ ሙያ እና ጥበብ እንዲጎለብት እና በባለሙያዎች መካከል ማኀበራዊ ትስስር እንደሚያጠናክር ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር መመስረቱ በተደራጀ መልኩ ሙያዊ አስተዋጽኦ ለማድረግ እና የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር ጠቅላላ ጉባኤ ማህበሩን የሚመሩ አመራሮችን በመምረጥም መጠናቀቁ ተገልጿል።
ከአፋር ክልል ለሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የሚያሰባስቡ ተሳታፊዎች መረጣ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል--ኮሚሽኑ
Dec 1, 2023 52
ሰመራ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፦ከአፋር ክልል ለሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የሚያሰባስቡ ተሳታፊዎች መረጣ ከነገ ጀምሮ እንደሚካሄድ የኢትየጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር አይሮሪት መሐመድ አስታወቁ። ኮሚሽነር አይሮሪት ዛሬ በሰመራ ከተማ በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት በክልሉ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ለሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የሚያሰባስቡ ተወካዮች መረጣ ከኅዳር 22 ቀን 2016 ጀምሮ ይከናወናል። መረጣው የሚካሄደው ኮሚሽኑ ለተባባሪ አካላት በሰጠው ሥልጠና የተለዩ ተሳታፊዎች ከየወረዳዎቹ ከመረጧቸው 4ሺህ 320 ተሳታፊዎች መካከል መሆኑንም ገልጸዋል። በዚህም የክልሉን 48 ወረዳዎች የማህበረሰብ ክፍሎች የሚወክሉ 864 ተሳታፊዎች እንደሚመረጡ አስረድተዋል። እንደ ኮሚሽነሯ ገለጻ በመረጣው ሴቶች፣ ወጣቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የጎሳ መሪዎች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ አርብቶ አደሮች፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ተፈናቃዮችና መምህራን ይወከላሉ። ኮሚሽኑ የአጀንዳ አሰባሳቢ ተወካዮች መረጣው አካታችነትን፣ ግልጽነትን፣ አሳታፊነትንና ተዓማኒነት ያገናዘበ እንዲሆን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የማህበረሰቡ ተወካዮች መረጣ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፍ ያሳሰቡት ዶክተር አይሮሪት፣ በዚህም ለሀገራዊ ምክክር ስኬት አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል። ባለፈው ወር በክልሉ የተካሄደው የተሳታፊዎች ልየታ ክልሉ ላደረገው ትብብርና ተሳትፎ ኮሚሽነሯ አመስግነዋል። የኢትየጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፈው ወር በክልሉ የተሳታፊዎች ልየታ ያካሄደ ሲሆን፣ በሁሉም ወረዳዎች ለተሰማሩ ተባባሪ አካላትም የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠቱን ለማወቅ ተችሏል።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መስተጋብር እሴቶች እንዲጎለብቱ መሥራት ይገባናል-ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ
Dec 1, 2023 2
ሐረር፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያውያን የአብሮነትና የአዎንታዊ መስተጋብር እሴቶች እንዲጎለብቱ መሥራት ይገባናል ሲሉ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ አስገነዘቡ። በሐረር ከተማ 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በድምቀት ተከብሯል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት “የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ኢትዮጵያ የብዝሃነት አገር መሆኗን በተጨባጭ የሚያሳይ ነው።'' በዓሉ የተለያየ ቋንቋ፣ ባህልና ታሪክ ያላቸው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች አንድነታቸውን ያጠናከሩበት መሆኑንም አመልክተዋል። በተጨማሪም ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ እያገዘ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ያስታወቁት። አቶ ኦርዲን እንዳሉት የክልሉ መገለጫ የሆኑ የአንድነት፣ የአብሮነትና የአዎንታዊ መስተጋብር እሴቶች እንዲጎለብቱ ቀጣይነት ያላቸው ሥራዎች ማከናወን ይገባል። "የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በማህበራዊ መስተጋብሮቻችን ያለንን አንድነት በማጠናከር ለሀገር ብልጽግና መሥራት ይገባናል" ሲሉም ተናግረዋል። በክልሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማቃለልና ለሕዝብ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል። በተጨማሪም በተቋማት የሚታዩ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ በዓሉ ያስገኘውን ትሩፋት ማስቀጠል ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል። የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም በበኩላቸው የዘንድሮ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል “ብዝሃነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት!'' በሚል ቃል በክልሉ በልማትና በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር መቆየቱን አስታውሰዋል። ኅዳር 29 ለኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እውቅና የሰጠ ሕገ መንግሥት የፀደቀበት ዕለት መሆኑን ያስታወሱት አፈ ጉባዔው፤ በዓሉ የኢትዮጵያውያንን አንድነት ያጠናከረና እርስ በእርስ ያስተሳሰረ ነው ብለዋል፡፡ በዓሉ የህዝቦች የእኩልነት መብት በሕገ መንግሥት የተረጋገጠበት መሆኑን አስታውሰው፣ የክልሉ ሕዝብ በጅግጅጋ ከተማ በሚከበረው በዓል ላይ የሚታደሙ እንግዶችን ተቀብሎ እንዲያስተናገድም አስገንዝበዋል። በበዓሉ የተሳተፉት አቶ ቶፊቅ መሐመድና ወይዘሮ ነቢላ መሐመድ በበኩላቸው አብሮነትንና አንድነትን በማጠናከር በክልሉ የተጀመሩ የሰላምና የልማት ሥራዎችን ለማስቀጠል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የክልሉን ሕዝብ የልማት ጥያቄዎችን በተሻለ ለመመለስና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራም ጠይቀዋል። አገራዊ አንድነት የሰፈነባት የተሻለች ኢትዮጵያን መፍጠር በሚያስችል መልኩ በዓሉን ማክበር እንደሚገባም ተናግረዋል። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ታድመዋል።
የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነድ እያዘጋጀ ነው
Dec 1, 2023 34
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚያደርገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን ለማስቻል የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነድ እያዘጋጀ ነው። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ያዘጋጀውን ረቂቅ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነድ በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል። ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚሰሩ ሥራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ረቂቅ ሰነድ ተዘጋጅቷል። ይህም ወቅታዊ፣ ግልጽና ቀልጣፋ መረጃዎችን የመለዋወጫ ምህዳር ለማስፋት ያስችላል ነው ያሉት። የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነዱ በተለይም ኮሚሽኑ ለተለያዩ ባለድርሻና አጋር አካላቶች የሚያስተላልፋቸውን መረጃዎች በምን መልኩና ለማን ምን አይነት መረጃ መቅረብ አለበት የሚለውን ለማመላከት ወሳኝ ነው ብለዋል። በቀጣይ ኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነዱን ከዘርፉ ተዋናዮች የሚሰጡት ገንቢ ሃሳቦች በማዳበር ሥራ ላይ እንደሚውል ጠቁመዋል። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሻንቆ ደለለኝ በበኩላቸው የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነዱ የቀድሞ ተዋጊዎች ወደ ማኅበረሰቡ ሲቀላቀሉ በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆኑ የማኅበረሰቡን ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሰፊ እድል እንዳለው ገልጸዋል። የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ትልቅ ሃብትን የሚጠይቅ በመሆኑ አጋር አካላቶች በዚህ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማጠናከር የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ሰነዱ ጠቀሜታ እንደሚኖረውም አመላክተዋል።
ወጣቶች በግንባር ቀደምነት ለሰላም ዘብ ሊቆሙ ይገባል
Dec 1, 2023 37
ባህር ዳር፤ ህዳር 21 /2016 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላም ለማስፈን እየተደረገ ባለው የተቀናጀ ጥረት ወጣቶች በግንባር ቀደምትነት ለሰላም ዘብ ሊቆሙ እንደሚገባ የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ጋሻው ተቀባ ገለጹ። “ድንበር ተሻጋሪ የወጣቶች እንቅስቃሴ ለፓን አፍሪካኒዝም” በሚል መሪ ሃሳብ 17ኛ የአፍሪካ ወጣቶች ቀን በባህር ዳር ከተማ ዛሬ ተከብሯል። የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ጋሻው ተቀባ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ለአንድ አገር ሁለንተናዊ እድገት ሰላም ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ባጋጠመው የጸጥታ ችግር በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩን አውስተው፤ ለዘላቂ መፍትሄው ወጣቶች በተደራጀ አግባብ መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። በተለይም አስተማማኝ ጸጥታ ለማስፈን መንግስት በተቀናጀ አግባብ እያደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ ወጣቶች በግንባር ቀደምትነት ለሰላም ዘብ መቆም እንደሚገባቸው አመልክተዋል። ሃገር የምትገነባው በወጣቶች የበሰለ ሃሳብና ተግባር እንደሆነ ጠቅሰው፤ አሁን ላይ በክልሉ እየተስተዋለ ያለው ችግር እንዲፈታ በባለቤትነት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሰላምና ደህንነት ትምህርት ክፍል መምህርና ጽሁፍ አቅራቢ ዶክተር ፍቅርተ አዱኛ እንደገለጹት፤ ወጣቶችን ወደ አመራርነት በማምጣት የሰላም ተዋናይ እንዲሆኑ መስራት ያስፈልጋል። ወጣቶች የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ባህል በማዳበር መንቀሳቀስ እንዳለባቸውም አብራርተዋል። እንደ አማራ ክልል ወጣት በተለይም በዚህ ወቅት ሰለ ሰላም በስፋት መስራት የሚጠይቅበት ወቅት መሆኑንም ገልጿል። ሰላምን ለማረጋገጥ መንግስት ከሚያከናውናቸው ተግባራት ጎን ለጎን የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ እንደሆነ የገለጸችው ደግሞ ወጣት አኒሻ ወርቁ ናት። ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን ወጣቶች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ጠቅሳ፤ ወጣቶች የሚያነሷቸውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ መፍታት እንዳለበትም ጠቁማለች። በባህርዳር በተከበረው የአፍሪካ ወጣቶች ቀን መረሃ ግብር ላይ የከተማ አስተዳደሩ የአመራር አባላትና የከተማው ወጣቶች ተሳታፊ ሆነዋል።
በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን በአንድ ጥላ በማሰባሰብ ባህልና እሴቶቻቸው ጎልቶ እንዲወጣ አድርጓል-የሰመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች
Dec 1, 2023 37
ሰመራ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፦በዓሉ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን በአንድ ጥላ ስር ከማሰባሰብ ባለፈ ባህልና እሴቶቻቸው ጎልቶ እንዲወጣ ያደረገ ነው ሲሉ በአፋር ክልል የሰመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በዓሉ እርስ በርስ ለመተዋወቅ፣ አንድነትን ለማጠናከር እና እኩልነትን በተግባር ለማረጋገጥ የቻሉበት መሆኑንም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። 18ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በአፋር ከልል ደረጃ ሲከበር የተሳተፉ የከተማው ነዋሪዎች እንዳሉት፣ ባለፉት ዓመታት የተከበረው በዓል የሀገሪቱ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እርስ በርስ እንዲተዋወቁ አድርጓል። አንዱ የሌላውን ባህል እንዲያውቅና እንዲያከብር እንዲሁም ተደብቀው የነበሩ ቱባ ባህሎች አደባባይ እንዲወጡ ማድረጉን ገልጸዋል። በተጨማሪም እኩልነትን በተግባር ከማሳየት ባለፈ፤ የአገር ባለቤትነት ስሜት በብሔር ብሔረሰቦች መካከል መሠረት እንዲይዝ እያደረገ መሆኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የሠመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪ አቶ ኑሩ ደበሌ በየዓመቱ በሚከበረው በዓል ላይ እንደሚሳተፉ ገልጸው፣ በዓሉ የእርስ በርስ ትብብርን ለማጠናከር ይገኛል ብለዋል። ''ኢትዮጵያውያን እጅ ለእጅ ተያይዘን ለአገር ልማት በአብሮነት መጓዝ ይገባናል'' ያሉት አቶ ኑሩ፣ በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦች በአንድ ጥላ አንዲሰባሰቡ አስችሏል ብለዋል። የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ባህልና እሴቶች ቀደም ባሉ ሥርአቶች ተገቢ ትኩረት ሳይሰጣቸው መቆየታቸውን የገለጹት ደግሞ አቶ ሰይድ ሙክተባ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። ቀኑ መከበሩ ህዝቦች ባህልና አሴታቸውን እንዲያጎለብቱ፣ እኩልነትን በተግባር እንዲያረጋግጡና አብሮነትን እንዲያጠናክሩ አስችሏል ሲሉም ገልጸዋል። የማይታወቁ ብሔረሰቦች ባህልና ቋንቋቸው እንዲታወቅ ማድረጉንም ጠቁመዋል። የብሔር ብሔረሰቦችን ቱባ ባህል፣ ቋንቋና እሴቶች ለማጎልበት በዓሉ ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የገለጹት ደግሞ አቶ ሁሴን መሐመድ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። እንደ እሳቸው ገለጻ በዓሉ በየዓመቱ መከበሩ አንዱ ብሔር ከሌላው ጋር እንዲተዋወቅ፣ ተከባብሮ አንዲኖርና በአገራዊ ጉዳይ አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ እያደረገ ነው። የሠመራ ከተማ ነዋሪ ወጣት አሊ ሰለለ በበኩሉ በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በአብሮነት ደምቀው የሚታዩበት መሆኑን ገልጿል። በበዓሉ ብሔር/ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቋንቋቸውን፣ ማንነታቸው እና ቱባ ባህላቸውን በአብሮነት ሲያሳዩ የኢትዮጵያዊያን የተለያዩ መልኮች ይንጸባረቃሉ ያለው ወጣት አሊ፣ በዓሉ አብሮነትን ስለሚያጎለብት መጠናከር አለበት ብሏል። ዘንድሮ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ህዳር 29 ቀን 2016 ዓ.ም "ብዝሃነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ እንደሚከበር ታውቋል።
ኢትዮጵያና እስራኤል የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
Dec 1, 2023 58
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና እስራኤል የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር መስማማታቸው ተገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በውይይታቸው አምባሳደር ምስጋኑ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቆየ የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ተከታታይ የሀሳብ ልውውጥ ማድረግ እንደሚያስፈልግ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ግንኙነቱን ለማጎልበትም በቀጣይ የሁለትዮሽ አሰራሮችን መፈተሽ እና የፖለቲካ ምክክር ማድረግ እንደሚገባም አምባሳደር ምስጋኑ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር መመስረት ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የጎላ ጠቀሜታ አለው - አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ
Dec 1, 2023 71
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር መመስረት ለብሔራዊ ጥቅም መከበር የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገለጹ። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያየ ጊዜ አገራቸውን ለረጅም ጊዜ በልዩ ልዩ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ የነበሩ የቀድሞ እና አንጋፋ አምባሳደሮችን፣ ዲፕሎማቶችንና በአሁኑ ወቅት እያገለገሉ ያሉ የመሥሪያ ቤቱ ባለሙያዎችን ያካተተ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር ተመስርቷል። በማኀበሩ ምስረታ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ የአገራቸውን ብሔራዊ ጥቅም እና ክብር እንዲጠበቅ ያደረጉ አንጋፋ ዲፕሎማቶችን እና የአሁኑን ትውልድ ባለሙያዎች የሚያሰባስበው ማኀበር መመስረቱ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል። ማኀበሩ በውጭ ግንኙነት ሥራ ውስጥ በጥናት እና ምርምር፣ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን በማሳየት እንዲሁም ወጣቶችን በማሰልጠን የእውቀት ሽግግር በማድረግ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ አምባሳደሩ መናገራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል። በማኀበሩ ምሥረታ ላይ የተገኙ አንጋፋ ዲፕሎማቶች የሙያ ማኀበር መመስረቱ የዲፕሎማሲ ሙያ እና ጥበብ እንዲጎለብት እና በባለሙያዎች መካከል ማኀበራዊ ትስስር እንደሚያጠናክር ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር መመስረቱ በተደራጀ መልኩ ሙያዊ አስተዋጽኦ ለማድረግ እና የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ማኀበር ጠቅላላ ጉባኤ ማህበሩን የሚመሩ አመራሮችን በመምረጥም መጠናቀቁ ተገልጿል።
ከአፋር ክልል ለሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የሚያሰባስቡ ተሳታፊዎች መረጣ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል--ኮሚሽኑ
Dec 1, 2023 52
ሰመራ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፦ከአፋር ክልል ለሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የሚያሰባስቡ ተሳታፊዎች መረጣ ከነገ ጀምሮ እንደሚካሄድ የኢትየጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር አይሮሪት መሐመድ አስታወቁ። ኮሚሽነር አይሮሪት ዛሬ በሰመራ ከተማ በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት በክልሉ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ለሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የሚያሰባስቡ ተወካዮች መረጣ ከኅዳር 22 ቀን 2016 ጀምሮ ይከናወናል። መረጣው የሚካሄደው ኮሚሽኑ ለተባባሪ አካላት በሰጠው ሥልጠና የተለዩ ተሳታፊዎች ከየወረዳዎቹ ከመረጧቸው 4ሺህ 320 ተሳታፊዎች መካከል መሆኑንም ገልጸዋል። በዚህም የክልሉን 48 ወረዳዎች የማህበረሰብ ክፍሎች የሚወክሉ 864 ተሳታፊዎች እንደሚመረጡ አስረድተዋል። እንደ ኮሚሽነሯ ገለጻ በመረጣው ሴቶች፣ ወጣቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የጎሳ መሪዎች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ አርብቶ አደሮች፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ተፈናቃዮችና መምህራን ይወከላሉ። ኮሚሽኑ የአጀንዳ አሰባሳቢ ተወካዮች መረጣው አካታችነትን፣ ግልጽነትን፣ አሳታፊነትንና ተዓማኒነት ያገናዘበ እንዲሆን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የማህበረሰቡ ተወካዮች መረጣ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፍ ያሳሰቡት ዶክተር አይሮሪት፣ በዚህም ለሀገራዊ ምክክር ስኬት አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል። ባለፈው ወር በክልሉ የተካሄደው የተሳታፊዎች ልየታ ክልሉ ላደረገው ትብብርና ተሳትፎ ኮሚሽነሯ አመስግነዋል። የኢትየጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፈው ወር በክልሉ የተሳታፊዎች ልየታ ያካሄደ ሲሆን፣ በሁሉም ወረዳዎች ለተሰማሩ ተባባሪ አካላትም የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠቱን ለማወቅ ተችሏል።
ማህበራዊ
በሥራ ላይ የቆየውን የሙስና መከላከል ስትራቴጂ በመከለስ ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው - የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
Dec 1, 2023 21
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፦ በሥራ ላይ የቆየውን የሙስና መከላከል ስትራቴጂ በመከለስ ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ። "ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው፤ በኅብረት እንታገል" በሚል መሪ ኃሳብ 20ኛው አገር አቀፍ የፍትህ ተቋማት የፀረ-ሙስና ቀን የምክክር መድረክ ተካሂዷል። የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ጊዜ፤ ሙስና አገርን እድገት በመፈተን የፍትሕ ተቋማትን ተዓማኒነት አደጋ ላይ የሚጥል የሥነ-ምግባር ጉድለት ነው ብለዋል። ፍርድ ቤቶች ፍትሕ ሰጪ ተቋማት በመሆናቸው በዳኝነት ሂደት ሕዝብና መንግሥት የጣለባቸውን አደራ በፍጹም ታማኝነት በመወጣት ለሙስና ትግሉ አዎንታዊ ሚና መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። የፍትሕ ተቋማት በሙስና ወንጀል ተጋላጭነት የሚፈተኑ በመሆናቸው ጫናውን በመቋቋም አገራቸውንና ሕዝባቸውን በታማኝነት በማገልገል ተጠያቂነት የማስፈን አገራዊ አደራ እንዳለባቸው አስገንዝዋል። የሙስና ወንጀል በፍትሕ ተቋማት ላይ ጥያቄ የሚያስነሳ ከሆነ የፍርድ ቤቶችን ተዓማኒነት በማጉደል ዜጎች በፍትሕ ተቋማቱ ላይ እምነት እንዲያጡ ያደርጋል ብለዋል። ሙስናን መከላከል ካልተቻለ እድገትና ኢንቨስትመንት እንዲገታ በማድረግ ውጤታማነትና ፈጠራን በማዳከም በአገርን ህልውና ውስጥ እንደሚከት ገልጸዋል። በዚሁ መነሻነትም ፍርድ ቤቶች የሙስና ተጋላጭነትን በመቀነስና ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። ለዚህም በሥራ ላይ የቆየውን የሙስና መከላከል ስትራቴጂ በመከለስ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል የክለሳ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። የፌዴራል የሥነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ምክትል ኮሚሽነር እሸቴ አስፋው፤ ሙስናን ለመከላከል የሃብት ምዝገባ፣ የተጋላጭነት ጥናት፣ የሥነ-ምግባር ግንባታና ግንዛቤ ፈጠራ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የፍትሕ ተቋማት የሙስና ተጋላጭነት አመላካች የጥናት ውጤት መካሄዱን ጠቅሰው፤ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተጋላጭነት ጥናት ውጤቱን ተግባራዊ ለማድረግ የወሰደውን ተነሳሽነት አድንቀዋል። የመሬት ዘርፍ፣ የካሳ ክፍያ፣ የመንግስት ግዥ፣ ሕገ-ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ፣ የመንግስት አገልግሎት ግንባር ቀደም የሙስና ተጋላጭ ዘርፎች መሆናቸው አመላክተዋል። የሙስና ወንጀል ለመከላከል ከፍትሕና ተጋላጭነት ከሚስተዋልባቸው ተቋማት ጋር በመተባበር ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በመድረኩም አገራዊ የሙስና ተጋላጭነትን ዓለም አቀፋዊ ተሞክሮን የሚያመላክቱና የፍትሕ ተቋማት የሙስና ተጋላጭነትን የሚያሳዩ የመነሻ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ምክክር ተደርጎባቸዋል።
በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሥርጭት በስፋት በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የቅድመ መከላከል ስራ በትኩረት ይሰራል
Dec 1, 2023 35
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሥርጭት በስፋት በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የቅድመ መከላከል ስራው በትኩረት እንደሚሰራ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የዓለም ኤድስ ቀን "የማህበረሰብ መሪነት የኤች አይ ቪ ቫይረስ መከላከል" በሚል መሪ ሀሳብ በአለም አቀፍ ደረጃ ለ36ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ35ኛ ጊዜ ተከብሯል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የዓለም ኤድስ ቀን ሲከበር ህብረተሰቡ የኤች አይ ቪ ቫይረስ በመከላከል የመሪነት ሚናውን እንዲወጣ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ሚኒስቴሩ ለቫይረሱ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ አብራርተዋል፡፡ የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭት ምጣኔን በመከላከል ረገድ መንግስትና ማህበረሰቡ ባደረጉት ጥረት እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር በ2010 ከነበረበት 1 ነጥብ 26 በመቶ በ2022 ወደ 0 ነጥብ 91 በመቶ መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ቫይረሱ በደማቸው ይገኛል ተብሎ ከሚገመቱ ሰዎች መካከል 84 በመቶ የሚሆኑት ተመርምረው ራሳቸውን እንዲያውቁና ከነዚህም ውስጥ 98 በመቶው የጸረ-የኤች አይ ቪ መድሃኒት እንዲጠቀሙ ማድረግ ተችሏል። ነገር ግን አሁንም የቫይረሱ ስርጭት በስፋት የሚስተዋልባቸው አካባቢዎች በመኖራቸው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ስርጭቱን ለመግታት እንደሚሰራ ዶክተር ሊያ ተናግረዋል። በተለይ የመገናኛ ብዙሃን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም አጀንዳ በማድረግ በትኩረት መስራት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። በአለም አቀፍ ደረጃ ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱን ገልጸው፤ ችግሩን ለማጥፋት ግን አፍላ ሴት ወጣቶች ላይ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በጤና ሚኒስቴር የኤች አይቪ መከላከል እና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈጻሚ ፍቃዱ ያዴታ በበኩላቸው፤ የዓለም አገራት በ2030 ኤች አይ ቪ ኤድስ ለማኅበረሰቡ ሥጋት ወደ ማይሆንበት ደረጃ ለማድረስ ጥረት በማረግ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የተ.መ.ድ የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከል መርሃ ግብር (ዩ ኤን ኤድስ) ዳይሬክተር ፍራኮዝ ናዪሺሚ በበኩላቸው በኢትዮጵያ ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ባለፉት ዓመታት አመርቂ ስራዎች እንደተሰሩ ገልጸዋል። በተለይ የማህበረሰብ አቀፍ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ስራው የቫይረሱ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መጥቷል ብለዋል። በመድረኩ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ በዘርፉ የሚሰሩ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ አምባሳደሮች፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የኢንዱስትሪውን ፍላጎት በአግባቡ የተረዱ ባለሙያዎችን ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ነው
Dec 1, 2023 39
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- የኢንዱስትሪውን ፍላጎት በአግባቡ የተረዱ ባለሙያዎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ገለጸ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪና በኤሌክትሮ ቴክኖሎጂ ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቋል። ሥልጠናው በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪና ኤሌክትሮ ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን ከ15 የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የተውጣጡ 58 ሰልጣኞች ተሳትፈዋል። በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥልጠናና የተቋማት አቅም ግንባታ ሥራ አስፈጻሚ ሙህዲን አባሞጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ የኢንዱስትሪውን ፍላጎት በአግባቡ የተረዱ ባለሙያዎችን ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ይህንንም ተከትሎ ይህ የአሰልጣኞች ሥልጠና መዘጋጀቱን ጠቁመው ሥልጠናው በኢንዱስትሪ ውስጥ ያለውን ከባቢ በደንብ የተረዳ አሰልጣኝ ለማብዛትና በሰልጣኝና ገበያው በሚፈልገው የባለሙያ አይነት መካከል ክፍተት እንዳይፈጠር ያስችላል ነው ያሉት። ከዚህ ቀደም 500 የሚሆኑ ሰልጣኞች በተመሳሳይ ሥልጠና መውሰዳቸውን ገልጸው ይህ ሥልጠና በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በጀርመን የልማት ተራድኦ ድርጅት (ጂ አይ ዜድ) የኢትዮ-ጀርመን የትምህርትና ሥልጠና መርሃ-ግብር አስተባባሪ አሊ ሙሃመድ ካሃን በበኩላቸው ሥልጠናው በጀርመን መንግሥትና በአውሮፓ ኅብረት የገንዘብ ድጋፍ የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል። መሰል የተግባር ሥልጠናዎችን ተግባራዊ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመው ለዚህም የሁሉም አካላት የጋራ ጥረት ወሳኝ መሆኑን አመላክተዋል። ከሥልጠናው ተሳታፊዎች መካከል በንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አሰልጣኝ ምስጋና በላይ፤ ሥልጠናው ቀደም ሲል በንድፈ ሐሳብ ደረጃ ያላትን እውቀት በተግባር ያየችበት መሆኑን ገልጻለች። በቀጣይም ከዚህ ሥልጠና ያገኘችውን እውቀት ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ተናግራለች። ሌላኛው የአርሲ ነገሌ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ አሠልጣኝ ሲሳይ በቀለም መሰል ሥልጠናዎች በስፋት ሊሰጡ እንደሚገባ አመላክቷል። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪና ኤሌክትሮ ቴክኖሎጂ የኢንዱስትሪ የተግባር ልምድ ለወሰዱ አሰልጣኝ መምህራንና ለፕሮጀክቱ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት እውቅና ሰጥቷል።
ጽዳትን ባህሉ ያደረገ ትውልድ ለመገንባት ትምህርት ቤቶች ላይ በጋራ መስራት ይገባል
Dec 1, 2023 44
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፦ጽዳትን ባህሉ ያደረገ ትውልድ ለመገንባት ትምህርት ቤቶች ላይ በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ አስታወቀ። ኤጀንሲው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጋር በመሆን የ2016 ዓ.ም የትምህርት ቤቶች የጽዳት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አካሒዷል፡፡ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ለማ በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ እንዳሉት፣ በ2014 ዓ.ም ጽዳትን በተመለከተ ከትምህርት ቢሮ ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት መደረጉን አስታውሰዋል። በስምምነቱ መሰረትም በየዓመቱ የትምህርት ቤቶች ንቅናቄ በማድረግ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ላይ የጽዳት ስራ በስፋት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም የትምህርት ቤቶችን አካባቢ ጽዳት ከመጠበቅ ባሻገር ተማሪዎች ጽዳትን በተመለከተ ግንዛቤያቸው እንዲያድግ የሚያስችሉ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አመልክተዋል፡፡ በዚህም በርካታ ሞዴል ትምህርት ቤቶችን መፍጠር መቻሉን የጠቆሙት ዶክተር እሽቱ፣ ከነዚህ መካከል እቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ቆሻሻን ከመጸየፍ ባሻገር አካባቢውን የሚያጸዳ ትውልድ ለማፍራት ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው የጽዳት ልምምድ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ የጽዳት ስራን ባህሉ ያደረገ ትውልድ ለመገንባት ትምህርት ቤቶች ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ታጋይቱ አባቡ በበኩላቸው፣ ባለፉት ዓመታት በትምህርት ቤቶች ላይ በተደረገ የጽዳት ዘመቻ በርካታ ሞዴል ትምህርት ቤቶችን መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በዚህም በርካታ ትምህርት ቤቶችን ጽዱ፣ ውብና ማራኪ በማድረግ ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ ሃላፊዎቹ በትምህርት ቤቶች ላይ የሚደረገው የጽዳት ንቅናቄ በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ የተካሔደው እቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት ሲሆን የኤጀንሲውን ዋና ዳይሬክተር ጨምሮ ፣ የትምህርት ቢሮና የጉለሌ ክፍለ ከተማ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ኢኮኖሚ
የቻይና ኮንግረስ ፓርቲ አባላት ገላን የሚገኘውን ኤ ኤም ጂ ቡና ላኪ ድርጅትን ጎበኙ
Dec 1, 2023 22
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፣- የቻይና ኮንግረስ ፓርቲ የግብርናና የገጠር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ገላን የሚገኘውን ኤ ኤም ጂ ቡና ላኪ ድርጅት ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ሎሚ በዶና ሌሎች የምክር ቤት አባላትም ተገኝተዋል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ እንዳሉት፣ ኢትዮጵያ የተለያዩ ተወዳጅ ጣዕም ያላቸው ቡና በስፋት በማምረት ለተለያዩ አገራት በመላክ ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል። የምትልከው ቡና በጥራትም ሆነ በማምረት አቅም እየጨመረ ይገኛል ብለዋል። ኢትዮጵያ ቡና ከምትልክባቸው አገራት መካከል ቻይና ተጠቃሽ መሆኗን አስረድተው፤ የቻይና ባለሃብቶች በዘርፉ በስፋት ቢሰማሩ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አብራርተዋል። በቻይና ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ የግብርናና የገጠር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዱ ጂሃኦ በበኩላቸው በቻይና ገበያ የኢትዮጵያ ቡና እየታወቀ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ከጉብኝቱም የቻይና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በቡና ዘርፍ በስፋት መሰማራት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩን መገንዘባቸውን ገልጸዋል። የቻይና ባለሀብቶች በቡና ማቀነባበሪያ ዘርፍ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል።
በአማራ ክልል ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የመደገፍና የማበረታታት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 1, 2023 39
ጎንደር፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የመደገፍና የማበረታታት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ዶክተር አህመዲን መሃመድ ገለጹ። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር አህመዲን መሃመድ በጎንደር ከተማ የሚገኘውን አባይ ጋርመንት ፋብሪካ የምርት እንቅስቃሴን ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡ ዶክተር አህመዲን በዚሁ ጊዜ በክልል ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍና በማበረታታት በኩል በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የጨርቃ ጨርቃና አልባሳት አምራች ኢንዱስትሪዎች ከውጪ የሚገቡ የአልባሳት ምርቶችን በማስቀረት ሰፊ ሚና እንዳላቸው ጠቁመው፤ የግብዓት አቅርቦትና የገበያ ትስስር በመፍጠር ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ''የአባይ ጋርመንት ፋብሪካም ከውጪ የሚገቡ አልባሳትን በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት ሰፊ አቅም እንዳለው መገንዘብ ችለናል'' ብለዋል ዶክተር አህመዲን፡፡ ፋብሪካው በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች የተደራጀና በገበያ ተፈላጊ የሆኑ ጥራትና ተወዳዳሪነት ያላቸው አልባሳትን የማምረት አቅም አሟጦ እንዲጠቀም ድጋፍ ይደረጋልም ብለዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ በበኩላቸው፤ የፋብሪካው በአካባቢው መቋቋም ለስራ አጥ ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር የጎላ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች መጠናከርና መበራከት ከመሬት አቅርቦት ጀምሮ የተለያዩ የማበረታቻ ስርዓቶችን በመዘርጋት እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የፋብሪካው ዋና ስራ አስኪያጅ ማናየሽ ተሰማ እንደተናገሩት፤ ፋብሪካው ጂንስ ሱሪዎችንና ቲሸርቶችን ጨምሮ የተለያዩ አልባሳትን በማምረት ለሀገር ውስጥ ገበያ እያቀረበ ነው፡፡ ፋብሪካው ባለፈው ዓመት ለሀገር ውስጥ ገበያ ካቀረበው የአልባሳት ምርት ከአንድ ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጪ ምንዛሬ ማዳኑን ጠቁመው፤ ዘንድሮም በተመሳሳይ ዕቅዱን ለማሳካት በምርት ስራ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ ዘመኑ የደረሰባቸውን የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች በመጠቀም በተለያዩ ዲዛይኖችና የጥራት ደረጃዎች ልዩ ልዩ የአልባሳት ምርቶችን ለሀገር ውስጥ ገበያ እያቀረበ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ፋብሪካው በአሁኑ ወቅት 800 ለሚደርሱ ሰራተኞች ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው፤ በሙሉ አቅሙ ወደ ማምረት ሲሸጋገር ለ3 ሺህ ያህል ሰራተኞች የስራ እድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡ በጎንደር ከተማ የሚገኘው በአባይ ኢንዱስትሪ ልማት አክሲዮን ማህበር የአባይ ጋርመንት ፋብሪካ በ2012 ዓ.ም በ450 ሚሊዮን ብር ወጪ በክልሉ መንግስትና በባለሃብቶች ትብብር የተቋቋመ ነው።
በክልሉ ለተጀመሩ የልማት ስራዎች ስኬታማነት ሌብነትንና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የክልሉ ነዋሪዎች ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል
Dec 1, 2023 33
ጋምቤላ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፡- በጋምቤላ ክልል ለተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ስኬታማነት ሌብነትንና ብልሹ አሰራሮችን በመታገል ረገድ የሁሉም የክልሉ ነዋሪ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ። ‘‘ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው ፤በህብረት እንታገል’’ በሚል መሪ ሃሳብ የዓለም የፀረ- ሙስና ቀን በክልል ደረጃ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ተወካይና የፀረ- ሙስና ግብረ ሃይል ጸሃፊ አቶ ብረሃኑ ደጀኔ፣ በፓናል ውይይቱ ላይ እንዳሉት ሙስና የሀገርን ልማትና እድገት የሚገታ ችግር ነው ። ሙስናና ብልሹ አሰራሮች የሀገርን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴን የሚያናጋና ዜጎችን ለእንግልትና ለከፋ ድህነት የሚዳርግ አደገኛ ወንጀል መሆኑን ተናግረዋል። የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በሚፈለገው ልክ መግታት ካልተቻለ የህዝቡን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ እንደማያስችል ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በጋምቤላ ክልል ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በመታገል የታለመውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ግብ መሳካት ሁሉም ዜጋ የድርሻውን እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል። የክልሉ ስነ-ምግባርና ፀረ- ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳይመን ቱሪያል በበኩላቸው የሙስና ትግሉ ፍሬያማ ሊሆን የሚችለው የሁሉም ዜጋ ተሳትፎና ትብብር መጠናከር ሲችል መሆኑን ገልጸዋል። ስለሆነም በኮሚሽኑ እየተካሄዱ ለሚገኙት የፀረ-በሙስና ትግል መሳካት ህዝቡ የተቻለውን ሁሉ ድጋፍና ትብብር እንዲያደረግላቸው ጠይቀዋል። በተለይም የትምህርት ማስረጃዎች እንደ ክልል የማጣራት ስራ መጀመሩን ጠቁመዋል። በግንባታ ዘርፍና የተመዘበሩ ገንዘቦችን ለማስመለስ በተቋሙ ግብረ ኃይሉ በኩል እየተሰራ ነው ብለዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ኮንግ ጆክ በሰጡት አስተያየት ኮሚሽኑ የሚመዘበሩ የመንግስትና የህዝብ ሃብትን በማስመለስ ረገድ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ኮሚሽኑ በግንባታና በሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች በኩል የሚታዩ ብልሹ አሰራሮችን በማጥራት ረገድ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ የጠየቁት ደግሞ ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ደሳለኝ ብሩ ናቸው።
በጌዴኦ ዞን በተያዘው ዓመት ከ40 ሚሊዮን በላይ የእንሰት ችግኝ ይተከላል
Dec 1, 2023 43
ዲላ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን በተያዘው ዓመት ከ40 ሚሊዮን በላይ የእንሰት ችግኞችን ለመትከል የዘር ብዜት ስራ መጀመሩን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ። የብዜት ስራው በዞኑ ኮቾሬ ወረዳ ዛሬ በይፋ የተጀመረ ሲሆን በቀጣይ መጋቢትና ሚያዚያ ወራት ለተከላ የሚሆኑ ችግኞችን ለማዘጋጀት የዘር ብዜት ሥራው የሚረዳ መሆኑም ተገልጿል። የዞኑ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ታጠቅ ዶሪ በወቅቱ እንዳሉት፤ በዞኑ የእንሰት ልማትን በማስፋት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ዞኑን የእንሰት ችግኝ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው። በተለይ የእንሰት ልማት ስራን በቴክኖሎጂ በማገዝ ምርታማነትን ለማሳደግ እየታዩ ያሉ ጅምር ጥረቶችን ለማጠናከር እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም በተያዘው ዓመት ከ40 ሚሊዮን በላይ የእንሰት ችግኞችን ለመትከል መታቀዱን ጠቅሰው ባለፉት ሁለት አመታት ለ"አንድ አርሶ አደር መቶ የእንሰት ችግኝ" በሚል ሃሳብ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል። በተያዘውም አመት በእንሰት ልማት የተጀመሩ ጥረቶች እንዲሳኩ አርሶ አደሮችና ባለድርሻ አካላት በነቂስ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል። በወረዳው አርሶ አደሩ እንሰትን በስፋት እንዲያለማ በማድረግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥም በተጨማሪ ገቢ እያገኘ ነው ያሉት ደግሞ የራጴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምራት ዴልቦ ናቸው። በወረዳው አሁን ላይ የተጀመረው የእንሰት ሰብል ስራ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየታዩበት እንደሆነ ጠቅሰው በተያዘው አመት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። የራጴ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አማኑኤል ወርቁ በበኩላቸው እንሰት ከምግብነት በተጨማሪም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። በወረዳው እንሰትን በተናጠልና በስብጥር በማልማት የአርሶ አደሩን ገቢ ማሳደግ መቻሉን ጠቅሰው በተያዘው ዓመትም ከ2 ሚሊዮን በላይ ችግኝ ለመትከል የዘር ብዜት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል። እንሰት የግብርና ልማት ስራች መሰረት ነው ያሉት ደግሞ የወረዳው አርሶ አደር ይጨነቁ ቦጋለ ናቸው። ምርቱ ከምግብ ዋስትና ባለፈ ለአፈር ለምነት፣ ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት እንዲሁም ተረፈ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ እየተጠቀሙ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በተያዘውም ዓመት ከ1 ሺህ በላይ እንሰት ለመትከል ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም የዘር ብዜት ስራ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የቺካጎ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ስድስት ተቀራራቢ ፕላኔቶች ማግኘታቸውን ገለጹ
Nov 30, 2023 71
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 20/2016 (ኢዜአ)፦ ስድስት ተቀራራቢ ፕላኔቶች ማግኘት መቻላቸውን በአሜሪካ የቺካጎ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አስታወቁ። ተገኙ የተባሉት ፕላኔቶች በራሳቸው የጸሃይ ስርአት ዙሪያ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ስርአቱን የጠበቀና ሙዚቃዊ ስልት ያለው መሆኑንም ተመራማሪዎቹ ይፋ ባደረጉት ምስል ገልጸዋል። ኤች ዲ 110067 የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ፕላኔቶቹ ኮማ ቤሬኒሲስ ከተባለው የህብረ ክዋክብት ስብስብ በአንድ መቶ የብርሃን አመታት ይርቃሉ መባሉን ኔቸር የተባለውን የምርምር መጽሄት ጠቅሶ ዩ ፒ አይ በድረ ገጹ አስነብቧል። የፕላኔቶቹ መገኘት ስለፕላኔቶች አፈጣጠር እና ዝግመተ ለውጥ አዲስ እይታ ሊፈጥር ይችላል የሚሉት የጥናት ቡድኑ መሪ ራፋኤል ሊዩክ “መሰል ግኝቶች ኔፕቱን በተባለችው ፕላኔት ዙሪያ ያሉ አካላት እንዲታወቁ እድል ይፈጥራል” ማለታቸውን ዘገባው አስታውሷል። “ምድር ካለችበት የጸሃይ ስርአት ውጪ ያሉ ሌሎች ፕላኔቶች አፈጣጠር፣ ቆይታ፣ የተሰሩበት ነገር ውሃ ስለመያዛቸው እና ሌሎች ጉዳዮች የጥናቱ መነሻ እንዲሆን አስችሏል” ብለዋል ተመራማሪው። የአሜሪካው ብሄራዊ የጠፈር ምርምር ኤጀንሲ ናሳ ከአውሮፓ የጠፈር ጥናት ድርጅት ጋር በመሆን በተላኩት ሳተላይቶች የክዋክብቱን የብርሃን መጠን፣ ከሌሎች ከዋክብት ጋር ያላቸውን መስተጋብር መመልከት እንደተቻለም ተገልጿል። እንደ ተመራማሪዎቹ ገለጻ ፕላኔቶቹ እርስ በእርስ ያላቸውን ርቀት የሚያስጠብቁበት ሬዞናንስ የተባለው ስርአት ያላቸው በመሆኑ በጸሃይ ዙሪያ ያሉት በርካታ ክዋክብት በሚያደርጉት መሽከርከር የሚጋጩባቸው አጋጣሚዎች በእጅጉ አናሳ መሆኑን በዘገባው ተመላክቷል።
የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ችግር ፈቺና ፈርጀ ብዙ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለተጠቃሚዎች እያሻገረ ነው
Nov 29, 2023 217
ጂንካ፤ ህዳር 19/2016 (ኢዜአ)፡- የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ውጤታማ፣ ችግር ፈቺና ፈርጀ ብዙ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለተጠቃሚዎች ለማሻገር አትኩሮ እየሰራ መሆኑን ገለጸ ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ካሳሁን ጌታቸው እንዳሉት፤ ኮሌጁ ችግር ፈቺ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለማህበረሰቡ በማሸጋገር ተጠቃሚ ለማድረግ አልሞ እየሰራ ይገኛል። ኮሌጁ በአካባቢው የሚገኙ ያልተነኩ አቅሞችን ለመጠቀም የተጀመሩ ጥረቶችን ለማገዝ የማህበረሰቡን ድካም የሚቀንሱና ውጤታማነትን የሚያጎለብቱ ቴክኖሎጂዎች ማፍለቅና ማሸጋገር ላይ ዋናው ትኩረት አድርጎ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል ። በተለይ ኮሌጁ ''ኢትዮጵያ ታምርት'' በሚል መሪ ሀሳብ በተጀመረው አገራዊ ንቅናቄ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ማሽነሪዎችን በሀገር ውስጥ ምርቶች ለመተካት ባደረገው እንቅስቃሴ ውጤት እየተገኘ መሆኑን ጠቁመዋል። ለአብነት በኮሌጁ ከተሰሩ የፈጠራ ስራዎች መካከል ከ30 እስከ 40 ሜትር ጥልቅ ጉድጓድ መቆፈር የሚያስችል ማሽን መሰራቱን ያነሱት አቶ ካሳሁን ከውጭ ሲገባ ከሚጠይቀው ወጪ አንጻር እጅግ ዝቅተኛ በሆነ ዋጋ ለማህበረሰቡ እየቀረበ እንደሚገኝ ነው የተናገሩት። ኮሌጁ የአርሶ አደሮችን ድካም ለማቃለል ከፈጠራቸው ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች መካከል የበቆሎ መፈልፈያ፣ የገብስና የጥራጥሬ መፈተጊያ ማሽኖች ይገኙበታል። የገብስና የጥራጥሬ መፈተጊያ ማሽኑም በባህላዊ መንገድ ጤፍ፣ ማሽላና ሌሎች ሰብሎችን በመውቃት የሚገጥመውን የምርት ብክነት መቀነስ የሚያስችል ቴክኖሎጂ መሆኑን አመላክተዋል። በኮሌጁ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ባለሙያ አቶ እስጢፋኖስ እያሱ በኮሌጁ የፈለቁ ማሽኖች የኃይል አማራጭ ስላላቸው መብራት በሌለባቸው አካባቢዎች በነዳጅ የሚሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህም ከኃይል አቅርቦት ጋር የሚስተዋሉ ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችል ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂ ነው ያሉት። ማሽኑ የኃይል አማራጭ እንዲኖረው መደረጉ አርሶ አደሮች እና በግብርና ላይ የተሰማሩ ኢንቬስተሮች ማሽኑን በተለያየ ቦታ በማንቀሳቀስ መጠቀም እንዲችሉ ታስቦ እንደተሰራም አስረድተዋል። በተለይ ተቋሙ የፈጠረው የጥራጥሬ መፈተጊያ ማሽን ስንዴ፣ ገብስ፣ ማሽላ እና ሩዝ መፈተግ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህም የአርሶ አደሩን ጊዜና ጉልበት ከመቆጠቡም ባሻገር የምርት ብክነትን ያስቀራል ብለዋል። በገጠር አካባቢዎች በስፋት የሸክላ ሥራ የሚተገበርና አሰራሩም ሁዋላ ቀር በመሆኑ ከዘርፉ የሚገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም አነስተኛ መሆኑን የገለፁት አቶ እስጢፋኖስ፤ ስራው በሰው ጉልበት በመሰራቱ እጅግ አድካሚ እንደሆነም አንስተዋል። ኮሌጁ ይህን ችግር በማየት የሸክላ አፈር መፍጨት፣ ማቡካትና የተለያዩ ቅርፆችን እንዲይዝ የሚያደርግ ዘመናዊ የሸክላ መስሪያ ማሽን መስራት ችሏል ብለዋል። ኮሌጁ የእርሻ ስራውን ለማዘመን እና የከብት እርባታውን አዋጭ ለማድረግ ከሚያግዙ ቴክኖሎጂዎች መካከል አነስተኛ የእርሻ ትራክተር እና የወተት መናጫ ማሽን እና ሌሎችንም ማፍለቅ መቻሉንም ገልጸዋል ። በፈጠራ ስራዎች ላይ ከተሳተፉ የኮሌጁ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ሙሉቀን አለማየሁ ለኢዜአ እንደገለፀው በኮሌጁ 30 በመቶ የንድፈ ሃሳብ፣ 70 በመቶ የሚሆነውን ደግሞ በተግባር ልምምድ እንደተማሩ ተናግሯል። የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአሁኑ ወቅት በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኮንስትራክሽን እና በሌሎች ተዛማጅ የትምህርት መስኮች 501 ነባር ተማሪዎችን እያሰለጠነ ሲሆን ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ደግሞ 600 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር በዝግጅት ላይ ይገኛል። ከመደበኛ የመማር ማስተማር ሰራው ጎን ለጎን 1 ሺህ ለሚሆኑ ሰልጣኞች በገበያ አዋጭነትና ስራ ፈጠራ ላይ አጫጭር ስልጠናዎችን ለመስጠት መዘጋጀቱንም ከኮሌጁ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የ5-ጂ ሞባይል ኔትዎርክ መስፋፋት የዲጂታል ልማትን ከማፋጠን ባለፈ ሀገራዊ የምጣኔ ኃብት እድገትን ለማረጋገጥ ሚናው የላቀ ነው
Nov 29, 2023 75
አዲስ አበባ ፤ህዳር 19/2016 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ የአምስተኛው ትውልድ (5-ጂ) የሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት መስፋፋት የዲጂታል ልማትን ከማፋጠን ባለፈ ሀገራዊ የምጣኔ ኃብት እድገትን ለማረጋገጥ ሚናው የላቀ መሆኑን የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ኢትዮ-ቴሌኮም የአምስተኛውን ትውልድ (5-ጂ) የሞባይል ኔትዎርክ በጅግጅጋ ከተማ በይፋ አስጀምሯል። የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ፤ በማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በዓለም ላይ እጅግ ፈጣን የሚባለውን የአምስተኛው ትውልድ (5-ጂ) የሞባይል ኔትዎርክ ኢትዮጵያ መጠቀም ጀምራለች ብለዋል። የአምስተኛው ትውልድ (5-ጂ) ኔትዎርክ ተጠቃሚ ከሆኑ የዓለም አገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ መሆኗንም ጠቅሰዋል። የ5-ጂ ኔትዎርክ ቀደም ሲል በአዲስ አበባ እና አዳማ በይፋ መጀመሩን አስታውሰው፤ አሁን ላይ በሱማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ በመጀመሩ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል። በኢትዮጵያ የማስፋፋት ሥራው በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይም ተጠናከሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል። የአምስተኛው ትውልድ (5-ጂ) የሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት የማስፋፋት ሥራ ለዲጂታል ኢትዮጵያ እውን መሆን የላቀ አስተዋጽዖ እንዳለውም ገልፀዋል። የ5-ጂ ኔትዎርክ አገልግሎት በጅግጅጋ ከተማ መጀመሩም የንግድና የመረጃ ሥርዓቱን ለማሳለጥና የመንግሥትን አገልግሎት አሰጣጥ የሚያቀላጥፍ መሆኑን ጠቅሰዋል። የሱማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ኢብራሂም ኡስማን፤ የቴክኖሎጂው እውን መሆን በክልሉ ለተጀመሩ የልማት ሥራዎች መፋጠን እንዲሁም በተለያዩ ሴክተሮች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያግዝ መሆኑን ገልፀዋል። በጅግጅጋ ኢዜአ ካነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ራሁ ጠይብካስ እና አብዱረዛቅ ሐሰን የአምስተኛው ትውልድ (5-ጂ) የሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት መጀመር በንግዱም ይሁን በሌሎች አገልግሎቶች ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ ተደስተናል ብለዋል። የ5-ጂ የኔትዎርክ አገልግሎት በተለይም ለስማርት ሲቲ፣ ስማርት ትራንስፖርት፣ የትምህርት ሥርዓት፣ ለጤና፣ ለውሃ፣ የግብርና ልማት፣ ለንግድና የፋይናንስ ሴክተር፣ ለኢንዱስትሪ፣ ለስማርት የመንግሥት አስተዳደር እና ሌሎችም ሴክተሮች የላቀ አበርክቶ እንዳለው ይነገራል።
አብርሆት ቤተመጻሕፍት የቴክኖሎጂ እና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሰልጣኞችን ተቀበለ
Nov 28, 2023 83
አዲስ አበባ፤ ህዳር 18/2016 (ኢዜአ)፦ የአብርሆት ቤተመጻሕፍት አምስተኛ ዙር የቴክኖሎጂ እና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሰልጣኞችን ዛሬ ተቀብሏል። ለሰልጣኞቹም የቤተመጻሕፍቱ ዳይሬክተር ኢንጂነር ውብአየሁ ማሞ አቀባበል ያደረጉ ሲሆን የእንኳን ደህና መጣቹ መልእክትም አስተላልፈዋል። አብርሆት ቤተመጻሕፍት ቀደም ሲልም በአራት ዙሮች 500 ሰልጣኞችን የተቀበለ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በአሁኑ ዙር የከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ መስፈርቱን ያሟሉ 200 ተማሪዎችን በመቀበል ለ4 ወራት የሚሰጠውን ስልጠና እንዲቀላቀሉ ተደርጓል። እነዚህ ተማሪዎች በቆይታቸው Data Structure ፣ Algorithm እንዲሁም የ Arteficial Intelligence ስልጠና እንደሚወስዱ ተገልጿል። ሰልጣኞቹ የተማሩትን የቴክኖሎጂ እውቀት በመጠቀምም ችግር ፈቺ አንዲሁም አለምአቀፋ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችላቸው መሆኑን አብርሆት ቤተመጻሕፍት ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል።
ስፖርት
በአዲስ አበባ ከተማ የቦክስ ስፖርት ውድድርን ለማስፋት እየተሰራ ነው
Dec 1, 2023 49
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፦ በአዲስ አበባ ከተማ የቦክስ ስፖርት ውድድር ለማስፋት በዘርፉ ስመ ጥር ስፖርተኞችን ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ገለፀ። "አዲስ ቦክስ ውድድር" በሚል ስያሜ የቦክስ ስፖርት ውድድር ትናንት ምሽት ላይ በአዲስ አበባ ከተማ ተከናውኗል ። በሁለቱም ፆታዎች ከ54 እስከ 81 ኪሎ ግራም ውድድር ተካሂዷል። በታዳጊዎች 54 ኪሎ ግራም ልዑልሰገድ ወንዱ አማኑኤል ታምራትን ሲረታ በአዋቂ ሴቶች 54 ኪሎ ግራም ሀገሪ እማኙ ሮማን አሰፋን አሸንፋለች። በተመሳሳይ በአዋቂ ወንዶች 54 ኪሎ ግራም ፍትዊ ጥኡማይ ዳዊት በቀለን ማሸነፍ ችሏል። በ57 ኪሎ ግራም የወንዶች ውድድር በዘንድሮው የኦሊምፒክ ማጣሪያ ከአፍሪካ ተወዳዳሪዎች ጋር ተፋልሞ ለአገሩ የብር ሜዳልያ ይዞ የተመለሰው ፍቅረ ማርያም ያደሳ ቢላል አስራርን አሸንፏል። በ63 ነጥብ 5 ኪሎ ግራም አዋቂ ወንዶች መስፍን ብሩና አብርሃም ዓለም ፍልሚያቸውን ያካሄዱ ሲሆን በመስፍን ብሩ አሸናፊነት መጠናቀቅ ችሏል። የውድድሩ የመጨረሻ ምድብ በሆነውና ብርቱ ፉክክር የታየበት 81 ኪሎ አዋቂ ወንዶች ፍልሚያ ሰይፉ ከበደ ከናትናኤል ነዋይ ጋር ተፋልሞ ማሸነፍ ችሏል። በየምድቡ አሸናፊ ለሆኑ ቦክሰኞች የ15ሺህ ብር ሽልማት ሲበረከትላቸው ለተጋጣሚዎች ደግሞ የ10ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ በላይ ደጀን በውድድሩ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር፤ ፤ እንደነዚህ ዓይነት ውድድሮች መዘጋጀታቸው ስፖርቱን እንደሚያነቃቃ ገልፀዋል። በዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች አገርን ወክለው የሚወዳደሩ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እንደሚረዳም ተናግረዋል። በከተማው የሚገኙ የስፖርት ማኅበራትን በመደገፍና ከባለድርሻ አካላት፣ ከባለሃብቶችና ስፖርትን ከሚወዱ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመስራት የቦክስ ውድድሮች በከተማ ደረጃ በስፋት እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት ኢንጂነር አስቻለው ኃይለማርያም በበኩላቸው የቦክስ ስፖርት እየተዳከመ መምጣቱን ገልፀዋል። ስለሆነም የቦክስ ስፖርት እንዲነቃቃና አገርን በኦሊምፒክ የውድድር መድረክ የሚወክሉ ስፖርተኞችን ለማፍራት የቦክስ ውድድሮችን በስፋት ማከናወን እንደሚገባ ተናግረዋል።
በስፖርት ማህበራዊ ትስስርን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም መጠቀም ይገባል
Nov 30, 2023 66
አሶሳ፤ ህዳር 20/2016 (ኢዜአ)፡- በስፖርት ማህበራዊ ትስስርን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም መስፈን መጠቀም ይገባል ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዋና አፈጉባኤ ዶክተር ተመስገን ዲሳሳ አስገነዘቡ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 18ኛውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ በመተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ ዛሬ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሂዷል። የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ዶክተር ተመስገን ዲሳሳ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ስፖርት የሚያስገኘውን ሁለንተናዊ ጠቀሜታ ለዘላቂ ሠላም ማዋል ይገባል። "ስፖርት የህብረተሰቡን ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከር የላቀ ጠቀሜታ አለው " ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው በዚህም ዘርፉን ለዘላቂ ሰላም መስፈን መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የውድድሩ ዓላማም በዓሉን ምክንያት በማድረግ የእርስ በርስ ግንኙነትን ማጠናከር መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር የሱፍ አልበሽር ናቸው። በዚሁ በሶስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የግልገል በለስ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ተቋርጦ የቆየው የኢትየጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጀመራል
Nov 30, 2023 86
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 20 /2016 (ኢዜአ) በአለም አቀፍ ውድድሮች ምክንያት ባለፉት 27 ቀናት ተቋርጦ የቆየው የኢትየጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጀመራል፡፡ ዛሬ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ድሬዳዋ ከነማ ከወላይታ ዲቻ ፤ ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት አምበሪቾ ዱራሚ ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ ሊጉ ነገም ቀጥሎ የሚውል ሲሆን ዘጠኝ ሰዓት ኢትዮጵያ መድህን ከመቻል ፤ በአስራ ሁለት ሰዓት ሻሸመኔ ከተማ ከወልቂጤ ከተማ የሚጫወቱ ይሆናል። ጨዋታዎቹ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይካሄዳሉ፡፡ ሊጉን ቅዱስ ጊዮርጊስ በ13 ነጥብ ሲመራ ሻሸመኔ ከነማ በአንድ ነጥብ የሊጉ መጨረሻ ላይ ተቀምጧል፡።
ፌዴሬሽኑ ለክልሎችና ክለቦች ማጠናከሪያ ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ ማበረታቻ ሽልማት ሰጠ
Nov 27, 2023 99
መቀሌ ፤ ህዳር 17/2016 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለክልሎችና ክለቦች አትሌቲክስ እንቅስቃሴ ማጠናከሪያ ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ ማበረታቻና ሽልማት ሰጠ። ፌዴሬሽኑ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የሚውል የሁለት ሚሊዮን ብርም ድጋፍ አድርጓል። ፌዴሬሽኑ ሽልማቱንና ድጋፉን ያደረገው በመቀሌ ከተማ ባካሄደው 27ኛ ጠቅላለ ጉባዔ ማጠቃለያ ላይ ነው። ድጋፉ የተሰጠው ስምንት ክለቦች፣ ሁሉም ክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች በዘርፉ ያደረጉትን እንቅስቃሴ በመገምገም መሆኑ ተመላክቷል። በዚህም ከፍተኛው 300 ሺህ ብር፣ ዝቅተኛው ደግሞ 40 ሺህ ብር ለክለቦቹ እና ለክልሎቹ ተሰጥቷቸዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ለክለቦቹና ለክልሎቹ የማበረታቻ ሽልማትና ድጋፍ የተደረገው አትሌቲክስን ለማስፋፋትና ለማጠናከር የሚያደርጉትን ጥረት ለማገዝ መሆኑን ተናግራለች። በእያንዳንዱ ክልልና ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የስፖርት አመራሮችና አሰልጣኞች ለዘርፉ ልማት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲያጠናክሩም አሳስባለች። የክለቦች፣ የክልሎችና የከተማ አስተዳደር የስፖርት አመራሮችና አሰልጣኞች ፌዴሬሽኑ የሰጣቸውን ድጋፍ የውስጥ አቅማቸው ለማጎልበትና ተተኪ አትሌቶች በፕሮጀክት አቅፈው ለማሰልጠን እንደሚረዳቸው ለኢዜአ ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እያለ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የሁለት ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ድጋፉን ከረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ተቀብለዋል። አቶ ጌታቸው ፌዴሬሽኑ ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን በማቅረብ ኢትዮጵያውያን በድርቁ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
አካባቢ ጥበቃ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኩባው ፕሬዝዳንት ሚግዌል ዲያዝ-ካናል ጋር ተወያዩ
Dec 1, 2023 60
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኮፕ28 ጉባኤ ጎን ለጎን የኩባውን ፕሬዝዳንት ሚግዌል ዲያዝ-ካናልን አነጋገሩ። ሁለቱ መሪዎች የአለም የአየር ጠባይ ለውጥ ኃላፊነትን፣ የሁለትዮሽ ትብብርን እና የብሔራዊ ልማት ጉዳዮችን የተመለከተ ውይይት ማድረጋቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ጠቁሟል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኮፕ28 ጉባኤ ጎን ለጎን የኩባውን ፕሬዝዳንት ሚግዌል ዲያዝ-ካናልን ያነጋገሩት በኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መካነ ርዕይ/ፓቪሊዮን/ ነው፡፡
ምክር ቤቱ የአበባ አልሚ ድርጅቶች የኬሚካል አያያዝና አወጋገድ እንዲስተካከል አሳሰበ
Dec 1, 2023 41
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፡-በአበባ አልሚ ድርጅቶች የሚታየውን የኬሚካል አያያዝና አወጋገድ ክፍተት እንዲስተካከል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በግብርና ሚኒስቴር የአበባ እርሻ ልማት ምርታማነትና የአካባቢ አያያዝ ስርዓት ውጤታማነት የ2014/15 የክዋኔ ኦዲት ላይ ውይይት አካሂዷል። በውይይቱ ላይ የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ሀራሬ ሞሲሳ እንዳሉት የግብርና ሚኒስቴር የአበባ ልማት በሚካሄድባቸው ስፍራዎች የአካባቢ ብክለት መከላከል ላይ ትኩረት አድርጎ ሊሰራ ይገባል። ለአበባ እርሻ ጥቅም ላይ የሚውሉ ኬሚካሎች የአያያዝ እና የአወጋገድ ክፍተት የሚያደርስውን ተዕጽኖ ለመፍታት በጥናት የተመሰረተ ምላሽ መስጠት እንደሚገባውም ነው የተናገሩት። በተለይ በአካባቢዎቹ ብክለትን ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች በተጠናከረ ሁኔታ ሊተገበሩ እንደሚገባም ተናግረዋል። በክዋኔ ሪፖርት ግኝት ላይ ከአበባ ልማት እርሻዎች የሚወጣ ኬሚካል በሰውና በእንስሳት ጤና ላይ ጉዳት ማድረሱ የተገለጸ በመሆኑ ይህን ችግር ለመፍታት በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሰረት ዳምጤ በበኩላቸው የክዋኔ ኦዲቱን ለማስተካከል የተደረገው ጥረት አበረታች መሆኑን አንስተው በዘርፉ የህግ-ማዕቀፍ በማውጣት ሊተገበር እንደሚገባ ተናግረዋል። ከአበባ እርሻ የሚለቀቁ ኬሚካሎች በትክክል እያደረሱ ያለውን ጉዳት ማጣራት እና በአካባቢው ካሉ አርሶ አደሮችን ጋር በቅርበት መስራት ይገባል ሲሉ አክለዋል። በቀጣይ ለእርሻው የኢንቨስትመንት ፍቃድ ሲሰጥ ከውሃ አካላት አካባቢዎች ራቅ ያሉ ቢሆኑ ተመራጭ መሆኑን አንስተዋል። በሰራተኛ የስራ ደህንነት ላይ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባም ገልጸው፤ ምርቱ በሚመረትበት ቦታ ላይ ከስር የፕላስቲክ ንጣፍ በሁሉም ፋብሪካዎች ላይ ሊደረግ እንደሚገባ ተናግረዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር መለስ መኮንን እንዳሉት ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የግብርናና የገጠር ልማት ማሻሻያ ፖሊሲ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል። ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግና ተግዳሮቶችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም ገልጸዋል። አሁን ምርት ላይ ከሚገኙት 63 ፋብሪካዎች ውስጥ 41 የሚሆኑት ላይ የፍሳሽ አወጋገድን ለማጣራት የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱን አክለዋል። ለግብርናው ዘርፍ የሚገቡ ኬሚካሎች የተመዘገቡ እና ቁጥጥር የሚደረግባቸው መሆኑን አስታውሰዋል። ወደ አገር ውስጥ ከገቡም በኋላ በአግባቡ እንዲወገዱ መመሪያ መኖሩን ገልጸው፤ መመሪያው መተግበሩን በመከታተል ችግሩን ለማስወገድ ጥረት እናደርጋለን ብለዋል።
የተቋማት ትኩረትና ቅንጅታዊ አሰራር ማነስ የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ላይ ጫና እያሳደረ ነው - የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት
Dec 1, 2023 45
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ) ፦የተቋማት ትኩረትና ቅንጅታዊ አሰራር ማነስ የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ መሆኑን የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ገለጸ። ብሄራዊ የብዝሃ ሕይወት ስትራቴጂና የድርጊት መርሃ-ግብር ብሄራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ የድህረ 2020 የብዝሃ ሕይወት ማዕቀፍ በተመለከተ ውይይት አካሂዷል። የድህረ 2020 የብዝሃ ሕይወት ማዕቀፍ ከሕዳር 28 እስከ ታህሳስ 10 ቀን 2015 ዓ.ም በካናዳ ሞንትሪያል በተካሄደው 15ኛው ዓለም አቀፍ የብዝሃ ሕይወት ጉባኤ ላይ የብዝሃ ሕይወት ሥምምነት አገራት በጋራ እንዲተገብሩት ታስቦ የጸደቀ ዓለም አቀፍ ማዕቀፍ ነው። የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መለሰ ማርዮ ኢትዮጵያ ከድህረ 2020 የብዝሃ ሕይወት ማዕቀፍ ጋር የሚጣጣም ብሄራዊ የብዝሃ ሕይወት ስትራቴጄና የድርጊት መርሃ-ግብር ለመቅረጽ የዝግጅት ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከፍተኛ የብዝሃ ሕይወት ሃብት ካላቸው 20 ቀዳሚ አገራት አንዷ መሆኗን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ ይህንን ትልቅ ሃብት ለመጠበቅ የበርካታ አካላት ቅንጅታዊ ስራ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ይሁን እንጂ በተቋማት ላይ የሚስተዋለው የትኩረትና ተባብሮ የመስራት ውስንነት የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ ነው ብለዋል። ለአብነትም የኢንቨስትመንት፣ የኢንዱስትሪ ልማት፣ የመንገድና መሰል መሰረተ ልማቶች የግንባታ ፈቃድ ከመሰጠቱና ወደ ትግበራ ከመገባቱ አስቀድሞ ከብዝሃ ሕይወት አኳያ የሚኖረውን አሉታዊ ተጽእኖ በአግባቡ ከማጥናትና ውሳኔ ከመስጠት አኳያ ጉድለቶች መኖራቸውን ተናግረዋል። በዚህም የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ጥበቃ የሚፈለገውን ያክል ውጤት አለማስመዝገቡን ገልጸዋል። በመሆኑም ተቋማት የሚስሯቸው ሥራዎች የብዝሃ ሕይወት ጥበቃን ከግምት ያስገቡ መሆናቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው ገልጸዋል። ተቋማቱ የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ዘለቄታዊ አጠቃቀምን የዕቅዳቸው አካል አድርገው በትኩረት መስራት አለባቸው ብለዋል። ብዝሃ ሕይወትን ከመጠበቅ አኳያ የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የአረንጓዴ አሻራ፣ የገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ ፕሮጀክቶች በተምሳሌትነት የሚነሱ ናቸው ብለዋል። ተቋማትም ይህንን ተሞክሮ በማስፋት ለብዝሃ ሕይወት ጥበቃ በጎ አስተዋጽዖ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል። የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ፈለቀ ወልደየስ በበኩላቸው ፖሊሲዎችና ዕቅዶች ሲወጡ ለብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ምላሽ መስጠትን ከግምት ውስጥ ሊያስገቡ እንደሚገባ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ በተለያዩ ምክንያቶች የብዝሃ ሕይወት ሃብት ላይ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን ጠቅሰው ኢንስቲትዩቱ በተቻለው መጠን ብዝሃ ሕይወትን ከጉዳት ለመታደግ እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም የብዝሃ ሕይወት ሀብት የማንበር፣ ዘለቄታ ያለው አጠቃቀም የማረጋጥና ከሀብቱ የሚገኘውን ጥቅም በፍትሃዊነት ማጋራት የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። የድህረ 2020 የብዝሃ ሕይወት ማዕቀፍ የዝግጅት ትግበራ ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶክተር ምስክር ተሰማ የብዝሃ ሕይወት ጥፋት ከአየር ንብረት ለውጥና ብክለት ባልተናነሰ ዓለምን እየፈተነ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም እ.አ.አ እስከ 2030 የሚተገበር አካታችና አሳታፊ የብዝሃ ሕይወት ስትራቴጂና የድርጊት መርሃ-ግብር ለማዘጋጀት ዕቅድ ተይዞ በእንቅስቃሴ ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ከዝግጅት እስከ ትግበራ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ በመሆኑ በተለይ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው ተቋማት የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ የትውልድ ጉዳይ መሆኑን ተረድተው ለፕሮጀክቱ ስኬት መረባረብ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። በዚሁ ረገድ ከ29 በላይ ተቋማትን በአባልነት የያዘው የብዝሃ ሕይወት ስትራቴጂና የድርጊት መርሃ-ግብር ብሄራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ሚናም የላቀ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአማራ ክልል በዘንድሮው የበጋ ወራት ለሚከናወነው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ከ376 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት ተለይቷል
Dec 1, 2023 53
ባህርዳር ፤ ህዳር 21/2016(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በመጭው ጥር ወር ለሚጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ከ376 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የመለየት ስራ መከናወኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ እስመለዓለም ምህረት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአፈር ለምነትን ለማሻሻልና የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው። ለዚህም በዘንድሮው የበጋ ወራት ከ9 ሺህ በሚበልጡ ተፋሰሶች ለሚከናወነው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ከ376 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የመለየት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል። በዚሁ የልማት ስራ ከ4 ነጥብ 5 ሚሊዮን የሚበልጡ አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ ጠቅሰው፤ ከነዚህ መካከልም ማሳን በመለካት ለትግበራ የሚያዘጋጁ ከ299 ሺህ በላይ ቀያሽ አርሶ አደሮች መሆናቸውን ገልፀዋል። ለቀያሽ አርሶ አደሮች በተግባር የታገዘ ስልጠና በየደረጃው ባሉ የግብርና ባለሙያዎች መሰጠት መጀመሩንም ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። ለልማት ስራውና ለቅየሳ ከሚያስፈልጉ ከአራት ሚሊዮን በላይ መሳሪያዎች ውስጥ እስካሁን ከግማሽ በላይ የሚሆነው መለየት መቻሉን አመልክተዋል። ወቅታዊ የፀጥታ ችግሩ እንዳለ ቢሆንም የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራው የህልውና ጉዳይ ሆኖ በልዩ ትኩረት እንደሚከናወንም አስገንዝበዋል። ለእቅዱ መሳካትም ባለድርሻ አካላት መረባረብ እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ አርሶ አደሩም ባለፉት ጊዜያት በተሰሩ ስራዎች የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል ሲባል በልማት ስራው በስፋት መሳተፍ እንዳለበት አሳስበዋል። በዘንድሮው ዓመት ለሚከናወነው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በዋግህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የደሃና ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሞገስ ታደሰ ናቸው። አካባቢያቸው በዝናብ እጥረት ለድርቅ የተጋለጠ በመሆኑ በየዓመቱ በበጋ ወራት ያከናወኑት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ በአካባቢው ተራቁቶ የነበረው መሬት ወደነበረበት እየተመለሰ መምጣቱን ገልጸዋል። በዘንድሮው የበጋ ወቅት ለሚከናወነው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራም ከወዲሁ ዝግጅት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። በማእከላዊ ጎንደር ዞን ላይ አርማጭሆ ወረዳ የግንድ መጣያ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ንጉሴ ማሩ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል ያለማናቸው ተፋሰሶች ለንብ ማነብና ለወተት ላሞች እርባታ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። ''የተራቆቱ አካባቢዎች በአጭር ጊዜ እንዲያገግሙ በየዓመቱ የሚያከናውኗቸው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ የአፈር መሸርሸርን ማስቀረት እንደቻለ ተናግረዋል። ከዚህም በላይ ለቤት እንስሳት መኖና ለንብ ማነብ ስራ አመቺ ሁኔታ በመፍጠሩ ዘንድሮም የልማት ስራው ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንደሚሆኑ ገልፀዋል። በክልሉ ባለፉት ዓመታት ከ7 ሚሊዮን ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ማከናወን እንደተቻለም የቢሮው መረጃ ያመለክታል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ መፍትሄዎች 30 ቢሊየን ዶላር ለመስጠት ቃል ገባች
Dec 1, 2023 83
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፡- የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ መፍትሄዎች ለሚደረገው ጥረት 30 ቢሊየን ዶላር ለመስጠት ቃል ገብታለች። የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ፕሬዝዳንት ሼህ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናሕያን የኮፕ 28 ጉባኤን በከፈቱበት ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን ለመዋጋትና ለችግሩ መፍትሄ ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ሀገራቸው 30 ቢሊየን ዶላር እንደምትለግስ ቃል ገብተዋል። ገንዘቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የሚያጋጥመውን የፋይናንስ ክፍተት ለመሙላትና ለማጠናከር እንደሚውል ተናግረዋል። ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ በንጹህ ሃይል ዘርፍ ላይ መዋዕለ-ነዋይን ለማፍሰስና የንጹህ ሃይል ሽግግር ለማድረግ በቂ የሆነ የፋይናንስ አቅርቦት እንቅፋት ሆኖ መቆየቱን ገልጸዋል። ኮፕ28 ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ መፍትሄዎች ሀገራት እንዲተባበሩ፣ አንዲወያዩና ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ በማሰብ የተዘጋጀ ጉባኤ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖዎችን ለመዋጋት የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በርካታ ስራዎችን መስራቷን ጠቅሰው፤ በተለይ የካርበን ልቀት መጠንን እ.አ.አ በ2030 በ40 በመቶ ለመቀነስና በ2050 ደግሞ ዜሮ ለማድረስ የተደረሰውን ስምምነት ለማሳካት በንጹህ ሃይል ዘርፍ ላይ መዋዕለ ነዋይ እያፈሰሰች እንደምትገኝ ገልጸዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዓመታዊ የአየር ንብረት ጉባኤ በዱባይ እየተካሄደ ሲሆን የሀገራት መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥ በተለይ በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት ላይ እያደረሰ የሚገኘውን ተጽእኖ ለመዋጋት የሚጠበቅባቸውን ፈንድ ለመመደብ ቃል ይገባሉ ትብሎ ይጠበቃል።
በአየር ንብረት መዛባት ምክንያት የሰው ልጆች ህልውና አደጋ ላይ ናቸው- ተመድ
Dec 1, 2023 47
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2016 (ኢዜአ)፦ የአየር ንብረት መዛባት በሰው ልጆች ህልውና ላይ አደጋ የደቀነ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስገነዘበ። የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ዱባይ እየተካሄደ ባለው ኮፕ 28 የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር አሁን ላይ የአየር ንብረት ለውጥ ለሰው ልጆች ህልውና አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል። በዱባይ እየተደረገ ባለው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ የሃገራት መሪዎች ችግሩን ለመከላከል የሚያስችል ተግባራዊና ተስፋ ሰጪ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ዋና ጸሃፊው ጥሪ አቅርበዋል። የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል የተሻለ ዓለም ለመፍጠር “በአመራር ብቃት፣ በአለምአቀፍ ትብብር እና በፖለቲካ ቁርጠኝነት ተግባራዊ እርምጃ እንውሰድ” ሲሉ ጥሪ ያቀረቡት ዋና ጸሃፊው፤ ከአመታት በፊት መከናወን የነበረባቸው በርካታ ውዝፍ ስራዎች አሉ ብለዋል። በማደግ ላይ ያሉ ሃገራት ባልፈጠሩት ችግር ጉዳት እያስተናገዱ እንደሆነ የገለጹት ጉቴሬዝ፤ የበለጸጉ አገራት ቀደም ሲል ቃል የገቡትን የፋይናንስ ድጋፍ ተግባራዊ እንዲያደርጉ አስገንዝበዋል። ድርጅቱ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2030 የታዳሽ ሃይል አጠቃቀም በሶስት እጥፍ እንዲያድግ ፍላጎት እንዳለው የተገለጸ ሲሆን ከተፈጥሮ ሃብት ከባቢ ጋር የሚስማሙት የንፋስ፣ የጸሃይ፣ የእንፋሎትና የውሃ ሃይል ምንጮች እንዲስፋፉ እያበረታታ መሆኑንም አሳውቋል። ድርጅቱ የአየር ንብረት መለወጥን ታሳቢ ያደረጉ ስራዎች ለመተግበር የገንዘብ ምንጮች እንዲገኙ አፋጣኝ እርምጃዎች ሊወሰዱ እንደሚገባ ማሳሰቡን የአናዶሉ ዘግቧል።
የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን በአፍሪካ ቀንድ ተጨማሪ የ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዮሮ አስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ አደረገ
Nov 30, 2023 73
አዲስ አበባ፤ ህዳር 20/2016(ኢዜአ):- የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን በአፍሪካ ቀንድ ለተከሰተው የጎርፍ አደጋ ተጨማሪ የ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዮሮ አስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ተጨማሪ ድጋፍ የሚያደርገው በሶማሊያ፣ በኢትዮጵያ እና በኬንያ በተከሰቱ የጎርፍ አደጋዎች ለተጎዱ ወገኖች መሆኑን የአውሮፓ ሲቪል ጥበቃ እና የሰብአዊ እርዳታ ስራዎች (ECHO) ትናንት ባውጣው መግለጫ አስታውቋል። ኮሚሽኑ በመግለጫው እንዳመለከተው፤ በሶማሊያ በአሁኑ ወቅት በተከሰተው የጎርፍ አደጋ በተለይም በጁባ ወንዝ ተፋሰስ አካባቢ ለሚገኙ ዜጎች የ2 ሚሊዮን ዮሮ ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚደረግም አመልክቷል። ይህም የገንዘብ ድጋፍ በሶማሊያ በቅርቡ በኤልኒኖ ምክንያት በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ለተጎዱ እና ለተፈናቀሉ ሰዎች ከዚህ በፊት ከተመደበው 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዮሮ ሰብአዊ እርዳታ በተጨማሪ የተሰጠ ነው ብሏል መግለጫው። ኮሚሽኑ በኢትዮጵያም በጎርፍ ለተጎዱ አካባቢዎች 1 ሚሊዮን ዮሮ ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጾ፤ ድጋፉም ጎርፉ ጉዳት ባደረሰባቸው አካባቢዎች መጠለያ ለመሥራት፣ አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለማከፋፈል፣ የውሃ ማጣሪያ እና ለህክምና አገልግሎት እንደሚውል አስታውቋል። የገንዘብ ድጋፉ በሶማሌ፣ ኦሮሚያ እና ደቡብ ክልሎች በአውሮፓ ህብረት የአደጋ ጊዜ ምላሽ ከጎርፉ በፊት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ለመሥራት ከተሰጠው የ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዮሮ አፋጣኝ እርዳታ በተጨማሪ የተሰጠ መሆኑን ኮሚሽኑ አመልክቷል። ይህም በቅርቡ በኢትዮጵያ ለተከሰተው የጎርፍ አደጋ ምላሽ አጠቃላይ የአውሮፓ ህብረት ያደረገውን የገንዘብ ድጋፍ ወደ 3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዮሮ እንደሚያሳድገው መግለጫው አመልክቷል።
ኢጋድ ና ሱዳን በሀገሪቱ የተፈጠረውን ቀውስ በሚረግብበት ሁኔታ ላይ ለመምክር ተስማሙ
Nov 27, 2023 119
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 17/2016(ኢዜአ)፡- ኢጋድ ና ሱዳን በሀገሪቱ የተፈጠረውን ቀውስ በሚረግብበት ሁኔታ ላይ ለመምክር ተስማሙ። የሱዳን ሉአላዊ የሽግግር መንግስት ሊቀመንበር አብዱልፈታህ አልቡርሃን እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ሊቀመንበር ወርቅነህ ገበየሁ በሱዳን ቀውስ ላይ አስቸኳይ ምክክር ለማድረግ መስማማታቸውን የሱዳን መንግስት አስታወቀ፡፡ አል ቡርሃን በሀገሪቱ የተፈጠረውን ቀውስ ለመፍታት በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ከኢጋድ ሊቀመንበር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ለመምከር ፍላጎታቸውን ያሳዩት ከጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ በተወያዩበት ወቅት ነው፡፡ አልቡርሃን እና የኢጋድ ሊቀመንበር ምክክራቸውን በሳውዲ አረቢያ እንደሚያደርጉ የተገለፀ ሲሆን የሱዳን ታጣቂ ሃይሎችና ፈጠኖ ደራሽ ሃይሉ በምክክሩ እንደሚገኙም የሱዳን መንግስት መግለጫ አመልክቷል፡፡ በመግለጫው የኢጋድ አስቸኳይ ጉባኤ የሱዳንን አሁናዊ የግጭት ሁኔታ እንዲፈታ ከሁሉም አካላት ስምምነት ላይ ተደርሷል ብሏል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ቅዳሜ እለት ባወጣው መግለጫ በሱዳን ያለውን ግጭት አውግዞ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በሀገሪቱ የተኩስ አቁም እንዲደረግ መጠየቁን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡
ሐተታዎች
"ድሽታ ግና'' የኣሪዎች የምስጋናና የምርቃት በዓል!
Nov 30, 2023 89
በጣፋጩ ሰለሞን (ኢዜአ) በኦሞ ሸለቆ አካባቢ በማጎ ብሔራዊ ፓርክ አቅራቢያ የሚገኙት አሪዎች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦች ውስጥ ይጠቀሳሉ፡፡ ''ኣሪ ኣፍ'' ወይም ''ኣሪኛ'' የተሰኘ የመግባቢያ ቋንቋም አላቸው፤ ከኦሞቲክ የቋንቋ ነገድ ይመደባል። የኣሪ ማህበረሰብ የኢኮኖሚ መሰረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ አካባቢውም ቆላ፣ ደጋ እና ወይና ደጋ የአየር ጠባይ አለበት። ኣሪዎች የቤት አሰራራቸው፣ የሙዚቃ ጥበባቸው፣ የአጨፋፈር ስልታቸው፣ አለባበስና አጋጌጣቸው እጅግ ማራኪና የቱሪስት ቀልብን የሚስብ ነው። እግር ጥሎት ወደ አካባቢው ያቀና እንግዳ ባይተዋርነት እንዳይሰማው የሚያደርገው የኣሪዎች የእንግዳ አቀባበል ባህል የሚደነቅ ነው። አሪዎች ለቤታቸው እንግዳ የሆነን ሰው ''አቦቶ፤ ደኣይቶ'' - ውይ በሞትኩልህ! እንደማለት ነው እያሉ ደረታቸውን እየደቁ ይቀበላሉ። ለእንግዳው አርደውና አብልተው ሲመሽ ደግሞ እግሩን አጥበው አልጋቸውን ለቀው መሬት አንጥፈው ያስተኛሉ። የራሳቸው የጊዜ ቀመር አቆጣጠር ያላቸው ኣሪዎች ''ሎንጋ'' በተሰኘው የታህሳስ ወር አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት ይቀበላሉ። ይሄው አዲስ ዓመታቸው ደግሞ ''ድሽታ ግና'' የሚል መጠሪያ ያለው ትልቅ ዓመታዊ ክብረ በዓላቸው ነው። የኣሪ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የባህል፣ የታሪክ፣ የቅርስ ጥናትና ልማት የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ዳኜ ገብሬ እንደሚሉት የአዲስ ተስፋና ወንድማማችነት ተምሳሌት የሆነው ድሽታ ግና በማህበረሰቡ ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው በዓል ነው። የብሔረሰቡ የዘመን መለወጫ የሆነው የ"ድሽታ ግና" በዓል የሁለት ቃላት ጥምር ሲሆን ''ድሽታ'' ምስጋና "ግና'' ደግሞ ምርቃትን ይወክላል። የ"ድሽታ ግና" በዓል አርሶ አደሩ የዘራው ዘር ፍሬ አፍርቶ ጎተራው፣ ከብቶች ተዋልደው ጋጥ ሲሞላና ቤቱ በበረከት ሲትረፈረፍ ፈጣሪን የሚያመሰግኑበት፤ በባህል መሪዎች ቡራኬ የሚሰጥበት ታላቅ የምስጋናና የምርቃት በዓል ነው። በባህሉ መሰረትም ወደ አዲሱ አመት ቂምና ቁርሾን ይዞ መሻገር አይቻልም። ስለዚህ ከበዓሉ በፊት በዳይና ተበዳይ "ይቅር" ተባብለው ቂም በቀልን ከአሮጌው ዓመት ጋር ሸኝተው በፍቅር አዲሱን ዓመት እንደሚቀበሉ ነው አቶ ዳኜ የሚናገሩት፡፡ በዚህም መሰረት አንድ የኣሪ ማህበረሰብ አባል በዓሉ ከመድረሱ በፊት "በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ያስቀየምኩት ካለ" በሚል በየቤቱ እየተዟዟረ ይቅርታ ይጠይቃል። በዚህ አጋጣሚ ምናልባት እስከ ህይወት መጥፋት ድረስ የሚደርስ በደል ከተፈፀመ በዳዩ ሽማግሌ ልኮ ፀፀቱን ገልፆ ተበዳይን ተማፅኖ ይቅርታ ይጠይቃል፤ ይቅርታም ይደረግለታል። በየቤቱ ይቅርታ የሚጠይቅበት ምክንያት ቂምና ቁርሾ ወደ አዲሱ ዓመት መተላለፍ ስለሌለበት ነው። ቂምና ቁርሾ በውስጡ ይዞ በዓሉን የሚያከብር አሊያም የበዓል ድግስ ደግሶ ጎረቤት ጠርቶ ማብላት በብሔረሰቡ ዘንድ በጥብቅ የተከለከለ እንደሆነ አቶ ዳኜ ይገልፃሉ። አንድ የኣሪ ማህበረሰብ አባል ዕርቅ ከፈፀመ በኋላ "አርሼ ጥሩ ምርት አግኝቻለሁ፤ ነግጄ አትርፊያለሁ፣ ከብቶቼ ጋጣ ሞልተውልኛል፣ ቤቴ በበረከት ተትረፍርፏል" ሲል ካገኘው ላይ ቀንሶ ድል ያለ ድግስ ይደግሳል። ድግሱ የተራበውን በማብላት፣ የተቸገረውን በመጎብኘት ፈጣሪ ላደረገላቸው በጎ ነገር ከሌሎች ጋር አብሮ ማዕድ በመቋደስ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርብበት እንደሆነም አቶ ዳኜ ይናገራሉ። የ"ድሽታ ግና" በዓል እሸት የሚቀመስበት ነው። በበዓሉ ዕለት የኣሪ ባላባቶች እሸቱን፣ ወተቱን፣ ማሩን ከቀመሱ በኋላ መጪው ዘመን የተባረከ፣ የጥጋብ፣ የሰላምና የጤና እንዲሆን ይመርቃሉ። የሰላምና የአብሮነት እንዲሁም ያለፈውን ዘመን በመተው በአዲስ ተስፋ እጅ ለእጅ በመያያዝ ወንድማማችነትን በማጠናከር ሰርቶ በመለወጥ እና ለሌላው መትረፍን ጭምር የሚያበረታታ በዓል ነው። የብሄረሰቡ ተወላጅ የሆኑት አቶ ፍቃዱ ጋሲ በእንደሚናገሩት፤ የ"ድሽታ ግና" በዓል የፍቅር፣ የአንድነትና የይቅርታ አስተምህሮ ያለው አብሮነትን የሚያጠናክር ነው። በዓሉ የተጣላውን የሚያስታርቅ የተራራቀውን የሚያቀራርብ በመሆኑ በየዓመቱ በጉጉት ይጠበቃል። የዕድገትና ለውጥ መሰረት ጭምር ተደርጎ የሚወሰድ ነው። የዘንድሮውን የ"ድሽታ ግና" በዓልም አብሮነትን፣ አንድነትን፣ መረዳዳትን በሚያጎላ ብሎም የባህሉን እሴት በጠበቀ መልኩ ለማክበር መዘጋጀታቸውን አቶ ፍቃዱ ይገልጻሉ። የ"ድሽታ ግና" በዓል ጠቃሚ ባህላዊ እሴቶች ያሉትና ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ የመጣ ነው። አሁንም በዓሉ ባህላዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር በማስተማር ሃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ነው በአጽንኦት የተናገሩት። የ"ድሽታ ግና" በዓል ከመድረሱ አስቀድሞ እናቶች ከእንሰት እና ከእንስሳት ተዋጽኦ የሚገኙ ለክብር እንግዶችና ለአባ ዎራዎች የሚቀርቡ ባህላዊ ምግቦችን የማዘጋጀት ስራ ላይ እንደሚጠመዱ የገለጹት ደግሞ የብሔረሰቡ አባል ወይዘሮ ደብሪቱ ኣዳዮ ናቸው። ወጣት ሴቶችና ወንዶች ደግሞ ቤት በማስዋብ እና ግቢ በማሳመር ስራ ላይ ይሳተፋሉ። በበዓሉ ወቅትም በቤት ውስጥ የተዘጋጁ ምግቦች በዓይነታቸው ተለይተው ይቀርባሉ። ጥሩ ምግብ ያዘጋጀችና ምግቧ ጣፋጭ የሆነላት ሴት በግጥምና በዜማ ትወደሳለች። የ"ድሽታ ግና" በዓል "የተጣሉትን በማስታረቅ፣ ከተቸገሩ ወገኖች ጋር ቤት ያፈራውን አብሮ በመቋደስ ፣የታመሙትን በመጠየቅ በጋራ የምናከብረው ልዩ በዓል ነው" ያሉት ወይዘሮዋ "ድሽታ ግና" ፍቅር፣ አንድነት እና በጎነት ጎልቶ የሚታይበት ዕለት እንደሆነም ነው የገለጹት። በድሽታ ግና በዓል "በዕርቅ የማይቋጭ ጥል፣ የማይድን ቁስል፣ የማይሽር ጠባሳ የለም" ብለዋል። በነዋሪው ዘንድም ለዘመናት ለዘለቀው ሰላምና አንድነት እንዲሁም ጠንካራ የስራ ባህል መሰረት ነው፡፡ የኣሪ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ኤሊያስ ቃሾ በበኩላቸው፤ በዓሉ ከኣሪ ማህበረሰብ አልፎ ለመላው ኢትዮጵያዊያን የሚሆን "በርካታ ጠቃሚ እሴቶችን በውስጡ የያዘ ነው" ሲሉም ይገልጻሉ። "ድሽታ ግና" ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነትን፣ መረዳዳትን እና አብሮነትን የሚያስተምር ህዝብ ለህዝብ የሚያቀራርብ ዕሴት ያለው በዓል ነው፡፡ የ"ድሽታ ግና" በአል ከጥንት አባቶቻችን ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ በዓል ቢሆንም የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ በመሆኑ ተደብቆ የኖረ ቱባ ባህል መሆኑን አንስተዋል። ሃላፊው እንዳሉት የ"ድሽታ ግና" በዓል ከለውጡ ማግስት በመንግስት በተሰጠው ትኩረትና ባገኘው ዕውቅና የአደባባይ በዓል ሆኖ በመከበሩ "የአገር ውስጥና የውጭ አገራት ቱሪስቶች እንዲጎበኙት በር ከፍቷል" ብለዋል። የ"ድሽታ ግና" በዓል እንደ ሌሎች ዕውቅና እንዳገኙ ክብረ በዓላት አድጎ፣ ጎልብቶ እንዲሁም ዕውቅና አግኝቶ ከአገራችን አልፎ የዓለም ቅርስ እንዲሆን የመላ ኢትዮጵያዊያንን እገዛ ያስፈልጋል። የዘንድሮው የድሽታግና በዓል ''ድሽታ ግና ለዘላቂ ሰላም እና ለፈጣን ልማት'' በሚል መሪ ሀሳብ በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች በድምቀት እንደሚከበር የተናገሩት ደግሞ የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ናቸው። በዓሉ "የመተሳሰብ፣ የመረዳዳትና የዕርቀ-ሰላም በመሆኑ የተጣላውን በማስታረቅ፣ የተቸገሩ ወገኖችን በመጎብኘትና ማዕድ በማጋራት ይከበራል" ብለዋል። ሰላምና ወንድማማችነትን የሚሰብከው "ድሽታ ግና" የአሮጌው ዘመን ማጠቃለያና አዲሱን ዘመን ብስራት ከአጎራባች ዞኖች እና ከመላው ኢትዮጵያዊያን ጋር ዕሴቱን በጠበቀ መልኩ በአደባባይ በጋራ ለማክበር አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል። የ"ዲሽታ ግና" ዕሴቶች አገር በቀልና በህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ያላቸው መሆኑን ያነሱት ዋና አስተዳዳሪው፤ እንደአገር ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲሁም የብልጽግና ጉዞን ለማጠናከር "ለተወጠኑ ግቦች ስኬት የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ልንጠቀምበት ይገባል" ብለዋል። ከወርሃ ህዳር አጋማሽ ጀምሮ ከቤተሰብ እስከ ኣሪ ባላባቶች ቅደም ተከተሉን ጠብቆ የሚከበረው የ"ድሽታ ግና" በዓል ታህሳስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ የአዲስ ዓመት ብስራት ይታወጅበታል። በዕለቱ በጂንካ ከተማ በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች በድምቀት ይከበራል። ''ዑሳ ዎም ዣዕሼ !'' እንኳን አደረሳችሁ!
ኢሬቻ የአብሮነት ማሰሪያ ሐረግ
Oct 6, 2023 674
ኢሬቻ የአብሮነት ማሰሪያ ሐረግ (አሸናፊ በድዬ) ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ከክረምት ወቅት መለያየትና መራራቅ በኋላ ሰዎች በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! የእውነትና የሰላም አምላክ! ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! ለምድራችን ሰላም ስጥ! ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!" ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 26 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 27 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" (በውሃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን በዓመቱ አጋማሽ ላይ የሚከበረው "ኢሬቻ ቱሉ" ደግሞ በተራራማ ቦታ የሚከበር ነው። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ሲሆን፤ የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመብቃቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ እዝነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። የኢሬቻ በዓል ከገዳ ሥርዓት ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው ሲሆን፤ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ለዘመናት ሲከበር የቆየ በዓል ነው። በዓሉ በዋናነት በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ፤ በቢሾፍቱ ከተማ በሆራ ሀርሰዲ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ታድሞ የሚከበር ቢሆንም በተለያዩ የኦሮሚያ ዞኖችና ወረዳዎች በድምቀት ይከበራል። የኦሮሞ ሕዝብ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው ፈጣሪ "ዋቃ" ምስጋናውን ለማድረስ የኢሬቻ በዓልን ያከብራል ይላሉ አባገዳዎች። የኦሮሞ ሕዝብ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ የኢሬቻ በዓልን ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲያከብር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይጎርፋል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል። ኢሬቻ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ሲሆን፤ የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ጭምር በመሆኑ ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኦሮሞ ሕዝብ ለሰላም ትልቅ ሥፍራ ይሰጣል። ሰላም ካለ ሁሉም ነገር አለ ብሎም ያምናል። በምርቃቱም "ቡና ፊ ነጋአ ሂንደቢና" ብሎ ይመራረቃል። ቡናና ሰላም አያሳጣችሁ ማለት ነው። ለዚህም ነው በኢሬቻ በዓል ለመላው የሰው ልጅ ሰላምና ደኅንነት ፈጣሪ የሚለመነው። ሳል ይዞ ስርቆት፤ ቂም ይዞ ፀሎት እንዲሉ አበው በኢሬቻ የተጣላ ታርቆ፣ ቂሙን ረስቶ በንጹህ ልቦና ፈጣሪ ንጹህ ወዳደረገው የውሃ አካል ይሄዳል፤ በዚያም ፈጣሪውን ያመሰግናል። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ…………………ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። ብሔር ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ለዚህም ነው ኢሬቻ ከኦሮሞ ሕዝብ አልፎ የመላው ኢትዮጵያውያን በዓልና መገለጫ ነው የሚባለው። በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ አገር የመጡ ልዑካን በዚህ በዓል ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። በዚህ ዓመትም የሦስት ጎረቤት አገራት ልዑካን በዚህ በዓል ላይ እንደሚታደሙ የተገለጸ ሲሆን፤ የኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገራት ተወካዮች እንደሚታደሙ ይጠበቃል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት ትልቅ አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!)
"በገበታ ለትውልድ" የሚለማው የደንቢ ሀይቅ
Oct 4, 2023 637
"በገበታ ለትውልድ" ስለሚለማው የደንቢ ሰው ሰራሽ ሃይቅ ምን ያህል ያውቃሉ? (በቀደሰ ተክሌ ከሚዛን አማን) ደንቢ ሃይቅ ሰው ሰራሽ ሃይቅ ሲሆን በእኛ የዘመን ቀመር በ1970ዎቹ የተሠራ ነው። በተፈጥሮ መስህቦች የተከበበው የደንቢ ሰው ሰራሽ ሃይቅ ለአካባቢው ብርሃንን ይፈነጥቅ ዘንድ የተሰራውን የቀድሞ የደንቢ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብን ተከትሎ የተፈጠረ ሃይቅ ነው። የደንቢ ሃይቅ ለአካባቢው ማህበረሰብ ባለውለታ ነው፤ የመጀመሪያውን የኤሌክትሪክ ብርሃን ያገኙበት ነውና። ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድቡ ከመልክዓ ምድሩ ጋር እንዲስማማ ተደርጎ የተገነባ በመሆኑ ውሃው ከላይ ወደ ታች በሁለት ምዕራፍ ቁልቁል እንዲወረወር ዕድልን ፈጥሮለታል። የመጀመሪያው የኤሌክትሪክ ሃይልን ለማመንጨት በዝግታ የሚወርደው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ሃይል አመንጭቶ ሲወጣ እጅግ ውብ የሆነ ፏፏቴን ፈጥሮ ወደ ታች የሚወርደው ነው። የደንቢ ፏፏቴ ከሃይቁ ወረድ ብሎ ስለሚገኝ "ደንቢ ሃይቅና ፏፏቴ" እየተባለ ይጠራል። ሃይቁን አይቶ ፏፏቴውን ሳያዩ መመለስ የማይቻል ነገር ነው። የደንቢ ፏፏቴ ከላይ ከዓለት ዓለት እየተጋጨ ሲወረወር የሚያሰማውን በግርማ ሞገስ በታጀበ ድምጽ፤ በተራራ ቀበቶ ተገምዶ ወደ ማረፊያ ቦታው ሲምዘገዘግ በለመለመው መስክ ላይ አሻግረው የሚቃኙት የተፈጥሮ ውበት ነው። ያሻው ወደ ተራራው ጫፍ ጠጋ ብሎ እንደ ጢስ በሚተነው የውሃ አካል ፊቱን እያስመታ አልያም ከሃይቁ ፊት ለፊት ራቅ ብሎ ተቀምጠው እየተመለከቱ መንፈስን የሚያድሱበት ውብ የፏፏቴ ሥፍራ ነው። ከላይኛው የግድቡ አናት ወደ ታችኛው ለመውረድ 640 ደረጃዎችን አቆልቁሎ መጓዝን ይጠይቃል። ይህ ትዕይንት ደግሞ የደንቢ ሃይቅ ሌላኛው መስህብ ነው። የደረጃዎቹን የመውጣትና የመውረድን ድካም አረንጓዴ ካባ የደረበው የሥፍራው ልምላሜ እንዲዘነጋ ያደርጋል። የደንቢ ሃይቅ አካባቢ ቀልብን ስቦ ድካምና ሌላ ሃሳብን አስትቶ ሃሴትን የሚያጎናጽፍ የተፈጥሮ ፀጋን የታደለ ነው። የደንቢ ሃይቅና ፏፏቴ ግርማ ሞገስ ምስጢሩ የአካባቢው ደን ነው። በረጃጅም እድሜ ጠገብ የሃገር በቀል ዛፎች የተከበበ ነው። በእምቅ ደኑ ውስጥ የሚገኙ አዕዋፋት ለሚገባ ለሚወጣው ሁሉ እንደየ ፀጋቸው ያዜማሉ። ጉሬዛዎችና ጦጣዎች ከዛፍ ወደ ዛፍ እየዘለሉ እጅ ይነሳሉ። ይህ አካባቢ የተጎናጸፈው የቱሪዝም ፀጋ ከብዙዎች ዐይን ርቆ ቆይቷል። አሁን ግን በቃ ብሎ ሚሊዮኖች ሊጎበኙት ጊዜው ተቃርቧል። አካባቢው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምሥረታን ተከትሎ ወደ ሥፍራው ጎራ ለሚሉ ሚኒስትሮችና የሃገር መሪዎች የማስተዋወቅ ሥራ በመሠራቱ "የገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክት አንዱ አካል ሊሆን ችሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ቦታው ድረስ በመሄድ፣ በማየትና ለዓለም ጭምር በማስተዋወቅ የደንቢ ሎጅ ግንባታን የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል። በመድረኩ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የሚለማው የደንቢ ሃይቅ ሎጅ ፕሮጀክት በአንድ ዓመት ተኩል የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚጠናቀቅ ነው። በተጨማሪም በደንቢ ሃይቅ ሎጅ አቅራቢያም ሌላው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠለት የአየር ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክት ይበልጥ አካባቢውን የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚያስችል ነው። የሎጅ ግንባታው ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባ፤ ደንቢ ላይ ያረፈ ጎብኚ ከ40 በላይ የሚፍለቀለቁ የዑሲቃ ፍል ውሃ ቦታዎችን፣ የጋርንናንሳ ተራራን እና ሌሎች የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ የቤንች ሸኮ ዞን የተፈጥሮ ፀጋዎችን በቅርብ ርቀት መጎብኘት ይችላል። የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሳሙኤል አሰፋ በርካታ የቱሪዝም ሃብቶችን በዙሪያው አቅፎ የያዘው ደንቢ በቅርቡ የቱሪዝም ኢኮኖሚ አነቃቂ ሃይል ይሆናል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በነደፉት የ"ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክት ሲለማ ከሃገር ውስጥ ባሻገር ከሃገር ውጭ በርካታ ጎብኚዎችን በማስተናገድ የውጭ ምንዛሬ የሚገኝበት ፕሮጀክት መሆኑንም ሳይዘነጉ። እንደዚህ አይነት ሃገራዊ ፕሮጀክቶች በአካባቢያቸው የተለመዱ አለመሆናቸውን ጠቅሰው የመንግስትን እይታና በአካባቢው ያለውን ሃገራዊ አቅም ወደ ኢኮኖሚ ለመቀየር ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑንም አድንቀዋል። የቤንች ሸኮ ዞን በርካታ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ መስህብ ሃብቶች እንዳሉት ገልጸው የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያለውን ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመቀላቀል መንግስት የከፈተውን መልካም አጋጣሚ መጠቀም እንደሚገባ ነው የጠቆሙት። ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት መሠረት ተቀምጦለት እየተገነባ ያለውን የሚዛን አማን ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ግንባታን መልካም አጋጣሚውን ለመጠቀም አንዱ ዕድል እንደሆነም ጠቅሰዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ ለመጎብኘት የሚመጡ እንግዶችን ቆይታ ለማራዘም እና ወደውት ተደስተው እንዲመለሱ ለማስቻል ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እናደርጋለን ያሉ ሲሆን በቅርብ ርቀት ያሉ የቱሪስት መዳረሻዎችን ምቹ የማድረግ ሥራም በትኩረት ይከናወናል ብለዋል። የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪው አቶ ያሬድ ካንጃ ደንቢ በቅርብ ርቀት ቢገኝም ያልለማ በመሆኑ ብዙዎች የመጎብኘት ዕድል እንዳላገኙ ተናግረዋል። ደንቢ ሃይቅ እና ፏፏቴ ከሃይቅነትና የቱሪስት መስህብነት ባሻገር በሥራ ዕድል ፈጠራም ጭምር ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አለው ነው ያሉት። የሎጁ መገንባት የዞኑን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ወደ ዓለም ገበያ ያስገባል የሚል ተስፋ መሰነቃቸውንም አቶ ያሬድ አልሸሸጉንም። "እንደ አካባቢው እምቅ የተፈጥሮ ሃብት አቅም አንጻር ይህ ጅምር ነው፤ በቀጣይ በርካታ ፕሮጀክቶችን እንጠብቃለን" ብለዋል።
የብርቅዬዎችን አምባ በዩኔስኮ መዝገብ ላይ እናቆይ!
Sep 30, 2023 857
በመሐመድ ረሻድ ባሌ ሮቤ(ኢዜአ) ኢትዮጵያ የብዙ ሕብረ ብሔራዊ ባህልና ማንነት ያሏቸው ሕዝቦች ሀገር ነች። የተፈጥሮ ገፅታዋ በልዩነት ውስጥ አንድነትን፣ በብዝሃነት ውስጥ ህብረትን አጎናጽፏታል። ከህዝቦቿ ጥምር ውበት ባለፈ ተፈጥሮ ያደላት የበርካታ ጸጋዎች ባለቤትም ናት። መስራት የሚገባውን ያክል ሳይሰራበት ቢቆይም አሁን ላይ እነዚህን ተፈጥሯዊ ሃብቶች የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማሳደግና የዘርፉን ተጠቃሚነትም ለማሳደግ እየተሰራባቸው ይገኛል። በዚህ ረገድ ሥሙ በቀዳሚነት ጎልቶ የሚነሳው ባለብዙ የተፈጥሮ ውበት ባለቤት የሆነውና "አንድ ፓርክ ብዙ ዓለማት (One Park Many World)" ተብሎ የሚታወቀው የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ አንዱና ዋነኛው ማሳያ ነው። በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ባሌ ዞን የሚገኘው ይህ ብሔራዊ ፓርክ ከአዲስ አበባ በ411 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። በድንቅ የተፈጥሮ ጸጋ የታደለው ይህ ስፍራ እንኳን ደህና መጣችሁ የሚያሰኝ ሃሴትን የሚሞላ ግርማ ሞገስን የተላበሰ ነው። ፓርኩ በሀገራችን ከሚገኙ 27 ብሄራዊ ፓርኮችና ሌሎች ጥብቅ ደን ስፍራዎች አንዱ ነው። በውስጡ በርካታ የብዝሃ-ህይወት ሃብትን የያዘና የጎብኚዎችን ቀልብ የሚስብ ነው። የደጋ አጋዘን፣ቀይ ቀበሮ፣ትልቁ ፍልፈል፣ የሳነቴ አምባ፣ የሀረና ጥቅጥቅ ደን ፓርኩ ከሚታወቅባቸው ብርቅዬዎች መካከል በዋነኞቹ ናቸው። የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በ2 ሺህ 150 ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት ላይ ተከልሎ የተመሰረተው በ1962 ዓ.ም ሲሆን በውስጡ ከ1 ሺህ 600 በላይ የተለያዩ የእጽዋት ዝርያዎች፣ ከ78 ዓይነት በላይ አጥቢ የዱር እንስሳት እና 300 የሚደርስ ዝርያ ያላቸው አዕዋፍን ይዟል። ከነዚህ መካከል 32 የእጽዋት ዝርያዎች እና በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ 31 ብርቅዬ የዱር እንስሳት እንደሚገኙበትም ከብሔራዊ ፓርኩ ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ ጥቂት ስለ ብሔራዊ ፓርኩ ጸጋዎች፦ ⦁ የሰማይ ላይ ደሴት(The Island in the Sky) - የሳነቴ አምባ የሳነቴ አምባ የተፈጥሮ ድንቅ ስራ የሚታይበት የፓርኩ ልዩ ገፅታ የሚንፀባረቅበት ነው። ስፍራው በአፍሪካ ካሉት ፕላቶዎች በስፋቱ 17 በመቶ የሚሸፍን ሜዳማና ትልቁ የአፍሮ አልፓይን አምባ ወይም የሰማይ ላይ ደሴት(The Island in the Sky) ነው፡፡ ይህ ውርጫማ ስፍራ የከፍተኛ ተራራዎች መገኛ ሲሆን፤ በሀገራችን በከፍታው ሁለተኛ የሆነውና ከባህር ጠለል በላይ 4ሺህ 377 ሜትር ከፍታ ያለው የቱሉ ዲምቱ ተራራ መገኛም ነው፡፡ የሳነቴ አምባ ከመልክዓ ምድሩ አቀማመጥ ባሻገር የዝናብ ውኃን የመሰብሰብና የማጥራት አቅም ያለው ድንቅ መልክዓ ምድር ነው። በተለይ በአካባቢው የሚገኙ የባሌ ፍልፈሎች ከጠላቶቻቸው ለማምለጥ ሲሉ የሚሰሯቸው እልፍ ጉድጓዶች ውኃው ወደ ከርሰ ምድር እንዲሰርግ ከፍተኛውን ሚና ይወጣሉ። ይህም ከ40 የሚበልጡ ጅረቶች ከፓርኩ እንዲፈልቁ ምክንያት ሆኗል። ጅረቶቹ አቅማቸውን በማሰባሰብ እንደ ዋቤ ሸበሌ፣ ገናሌ፣ ዌልመልና ዱማል የመሳሰሉ ትላልቅ ወንዞችም መነሻ ቦታ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ ሳነቴ የ'ውኃ ጋን' የሚል ስያሜንም እንዲያገኝ ምክንያት ሆኗል። ከሳነቴ አምባ የሚፈልቁት እነዚህ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች በዞኑ የደሎ መናና ሀረና ወረዳ ለሚገኙ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ የዘመናዊ መስኖ ልማት ምንጭ እየሆኑም መጥተዋል። በተለይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የግንባታ ሥራውን ከሶስት ዓመት በፊት ያስጀመሩትና ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ ከ11 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ የማልማት አቅም ያለው የዌልመል ዘመናዊ የመስኖ ልማት ፕሮጄክት አንዱ ማሳያ ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ በኬንያና ሶማሊያ የሚኖረው ከ30 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ህልውው ከዚህ አካባቢ በሚፈልቁ ተፋሰሶች ላይ የተመሰረተ መሆኑን በብሔራዊ ፓርኩ የዱር እንስሳት ክትትልና የምርምር ቡድን መሪ አቶ ሴና ገሼ ያስረዳሉ። ⦁ "የሀረና የተፈጥሮ ደን ሀብት" የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በሀገራችን በጥቅጥቅ ደን ሽፋኑ ከያዮ ደን ቀጥሎ የሁለተኛነትን ስፍራ የያዘው የሀረና የተፈጥሮ ደን ሀብት መገኛም ነው፡፡ ደኑ የፓርኩን 1ሺህ ካሬ ኪሎ ሜትር ገደማ ይሸፍናል፡፡ ከሀገራችን አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ለካርቦን ንግድ ታጭተው ህብረተሰቡ ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆን እያገዙ ከሚገኙ የሀገራችን ድንቅ ደኖች ውስጥም አንዱ ሆኗል። የሀረና የተፈጥሮ ደንን በአሳታፊ የደን ልማት አስተዳደር አርሶ አደሩን በ38 የደን ማህበራት በማደረጃት ባለፉት አራት ዓመታት በተከናወኑ ሥራዎች ከ179 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ከከርቦን ንግድ ሽያጭ መገኘቱን በኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት የባሌ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዕቅድ ክትትል የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ቀነዓ ያደታ ይገልጻሉ። የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በውስጡ ባሉት የእጽዋት እና የእንስሳት ብዝሃ ህይወት ሲታይ ከዓለም በ34ኛ፣ ከአፍሪካ ደግሞ በ12ኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በተለይ ፓርኩ በውስጡ ከሚገኘው እጽዋትና የእንስሳት ብዝሃ ህይወት በተጓዳኝ ለአዕዋፍ ዝርያ ካለው ምቹ ሁኔታ የተነሳ “Bird Site International” የተሰኘ ዓለም አቀፍ ድርጅት "በዓለም ከሚገኙ ምቹ የአዕዋፍ መገኛዎች አንዱ ስለመሆኑም አብነቱን ይሰጣል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ከላይ የተጠቀሱ እውናታዎችን ጨምሮ ሌሎች የፓርኩ እምቅ አቅሞችን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት እ.ኤ.አ. በ2009 በጊዜያዊ መዝገቡ ላይ ማስፈሩም ይታወሳል። መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ በርካታ ባለድርሻ አካላት ባለፉት ዓመታት ቅርሱ በቋሚነት በዩኔስኮ እንዲመዘገብ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን የፓርኩ ኃላፊ አቶ ሻሚል ከድር ያስታውሳሉ። በተለይ ፓርኩ በድርጅቱ በቋሚ የቅርስ መዝገብ ላይ እንዳይሰፍር ማነቆ ሆነው ከቆዩት መካከል ልቅ ግጦሽ፣ የሰደድ እሳት፣ ህገ ወጥ ሰፈራ ሲሆኑ፤ ችግሮቹ አሁንም ያልተሻገርናቸውና የሁሉንም ትኩረት የሚሹ ናቸው ይላሉ። በተለይ በፓርኩ አልፎ አልፎ የሚያጋጥመው ሰደድ እሳት የብርቅዬ የዱር እንስሳትን መኖሪያና ምግባቸውን ስለሚያሳጣቸው በቀጣይነት በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባም ያስረዳለሁ። ⦁ "ፓርኩን ለማቆየት የተከፈለ የህይወት መስዋዕትነት" ይህ የብርቅዬዎች አምባ ተጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ በተላይም የባሌ ህዝብ፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አያሌ መስዋዕትነት ከፍለዋል። በተለይ በ2007 ዓ.ም ፓርኩ ላይ ተነስቶ የነበረው የሰደድ እሳት በባሌ ህዝብ ዘንድ የማይረሳ ጠባሳ ጥሎ ማለፉን ነው አቶ ሻሚል ያስታወሱት። በግንዛቤ ማነስ ጭምር ግለሰቦች ለከብቶቻቸው የተሻለ መኖ ለማግኘት በማሰብና ለማር ቆረጣ በፓርኩ ክልል ውስጥ እሳት በመለኮስ ያስነሱትን ቃጠሎ ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር ለማጥፋት ጥረት ሲያደርግ ህይወቱን ያጣውን የፓርኩን ሰራተኛና የአካባቢ ተቆርቋሪ ወጣት ቢኒያም አድማሱን በማሳያነት አቅርበዋል፡፡ ወጣቱ የተፈጥሮ ሀብት ጀግና በሚል በፓርኩ ውስጥ የማስታወሻ ሀውልት ቆሞለታል። እንዲሁም በተጠናቀቀው የ2015 ዓ.ም የበጀት ዓመት የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ባካሄደው ዓመታዊ ግምገማ የተፈጥሮ ሀብት ጀግና ለሆነው ለቢኒያም አድማሱ ቤተሰቦች ዕውቅናና ሽልማት ሰጥቷል። እንዲያም ሆኖ ግን ጠባሳው በብዙ የአካባቢ ተቆርቋሪዎች ዘንድ ሁሌም የሚታወስ ነው፡፡ ይህ በብዝሃ ህይወት ስብጥሩና በአያሌ ጸጋዎች የተንበሸበሸው የብርቅዬዎች አምባ በቅርቡ በሳውዲ አረቢያ ሪያድ ተካሂዶ በነበረው 45ኛው የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የዓለም ቅርስ ጉባኤ ላይ በኢትዮጵያ ሁለተኛው ታላቅ የተፈጥሮ ቅርስና በዓለም ደግሞ 11ኛው ቅርስ በመሆን በቋሚነት መመዝገቡ ሁሉንም የአገሪቱን ዜጎች አስደስቷል። ፓርኩ በዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ለቅርሱ የሚደረግለትን ጥበቃ ለማጠናከርና መስህብነቱን ለመጨመር እድል እንደሚፈጥር የዞኑ ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሮብዳ ጃርሶ ይገልጻሉ። እንዲሁም ፓርኩ በዩኔስኮ እውቅና ማግኘቱ የቱሪስት ፍሰቱን በማሻሻል ከቱሪዝም የሚገኘውን ዓመታዊ ገቢ በማሳደግ ሀገርና ሕዝብ ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዕድል የሚፈጥር ነው ይላሉ። ቅርሱን በዩኔስኮ ማስመዝገብ ብቻውን ግብ አይደለም ያሉት ወይዘሮ ሮብዳ ህብረተሰቡ ተንከባክቦ ለዛሬ ያቆየውን ቅርስ በዘላቂነት መጠበቁ ላይ እንዲበረታም አሳስበዋል። በፓርኩ ላይ የሚደርሰውን ሰው ሰራሽ ጫና ሊቀነሱ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ ገቢራዊ እያደረጉ ከሚገኙ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት መካከል የፍራንክፈርት ዞሎጂካል ሶሳይቲ ድርጅት የባሌ ዞን ቅርንጫፍ አስተባባሪ አቶ አብዱርቃድር ኢብራሂም የፓርኩ የጥበቃ ሥራ የአካባቢውን ማህበረሰብ ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ይናገራሉ። በተለይ በፓርኩ አጎራባች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በፓርኩ ላይ እያደረሱሷቸው ያሉ ጫናዎችን ለመቀነስ ህይወታቸውን የሚመሩበት ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ተጽዕኖውን መቀነስ እንደሚቻል ያምናሉ። ፓርኩን በዩኔስኮ ቋሚ መዝገብ ላይ ለማስፈር የተደረገው የተቀናጀ ጥረት እንዳለ ሆኖ ይሄው ገጽታውና ክብሩ ተጠብቆ እንዲቆይ ከፍተኛ ጥረትና ቁርጠኝነትን እንደሚጠይቅም በአጽኖኦት ያስረዳሉ። ከአካባቢው ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ነፊሳ መሐመድ እንዳሉት ፓርኩን ለመጎብኘት ለሚመጡ የሀገር ውስጥና የውጭ አገር ጎብኝዎች የዕደ ጥበብ ቁሳቁሶችን በመሸጥ በሚያገኙት ገቢ ህይወታቸውን እየመሩ ናቸው። እንደሳቸው እምነት በአሁኑ ወቅት ፓርኩ በቋሚነት በዓለም ቅርስነት በመመዝገቡ ለቅርሱ የሚያደርጉትን ጥበቃ ይበልጥ እንዲያጠናክሩ መነሳሳትን የሚፈጥር ነው። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህርና በአካባቢ ሳይንስ ላይ ምርምር የሚያደርጉት አቶ አልይ መሐመድ እንዳሉት በፓርኩ አካባቢ የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከፓርኩ በሚፈለገው ደረጃ ተጠቃሚ ቢሆኑ የጥበቃውን ሥራ በእጅጉ ያቃልላል የሚል እምነት አላቸው። ይህ ደግሞ የባለቤትነት ስሜትን በሚፈለገው ደረጃ እንዲያዳብሩ የሚያደርግም ነው። በመሆኑም በፓርኩ ላይ እየደረሰ የሚገኘውን ጫና ለመቀነስ የአካባቢውን ማህበረሰብ ከብሔራዊ ፓርኩ በኢኮ-ቱሪዝምና ተያያዥ ጉዳዮች ተጠቃሚ በማድረግ የባለቤትነት አስተሳሰብን ማጎልበት እንደሚያስፈልግም ያስረዳሉ። በተለይ ለማህበረሰቡ አማራጭ የግጦሽና የሰፈራ ቦታ፣ የማገዶ፣ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች አማራጮች በቀጣይ እንዲቀርቡለት የማድረግ ስራ ቢሰራ በፓርኩ ላይ የሚደርሰውን ጫና ትርጉም ባለው መልኩ መቀነስ እንደሚቻልም ይመክራሉ። ከሀገር አልፎ የዓለም ቅርስ የሆነውን የብርቅዬዎች አምባ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በዩኔስኮ ቋሚ መዝገብ ውስጥ ለማቆየት የሚያግዙ ሥራዎችን ከወዲሁ አቅደው እየሰሩ መሆኑን የፓርኩ ኃላፊ አቶ ሻሚል ያስረዳሉ። ብሔራዊ ፓርኩን በሚያዋስኑ ወረዳዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ስለብዝሃ ህይወት ጥቅምና ተጓዳኝ ጉዳዮች በቂ ግንዛቤ አግኝተው በጥበቃው የድርሻቸውን እንዲወጡ ተከታታይነት ያለው የግንዛቤ ማዳበሪያ ሥራዎች እየተከወኑ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የዓለም ቅርስ የሆነው የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት መንከባከብና መጠበቅ የሚያስችሉ ሀገር በቀልና ዘመናዊ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ ፓርኩን በድርጅቱ ቋሚ መዝገብ ውስጥ ከማቆየት ባለፈ ከዘርፉ የሚገኘውን ዘላቂ ጥቅም ለማረጋገጥ ሁሉም የድርሻውን በቁርጠኝነትና በፅናት ሊወጣ ይገባል።
ትንታኔዎች
ከገበታ ወደ ገበያ
Sep 24, 2023 642
(ሰለሞን ተሰራ) ኢትዮጵያ ከ10 ሺ ዓመታት በፊት ከኒዮሊቲክ አብዮት ዘመን ጀምሮ የበርካታ አዝእርትና እንስሳት ሀብት መፍለቂያ ሆና ዛሬ ላይ ደርሳለች። ከዚያ ዘመን ጀምሮ የአገራችን ገበሬ በስራ ያካበተውንና በተፈጥሮ የተሰጠውን ችሎታ በመጠቀም ዘመናዊና ቴክኖሎጂ በወለዳቸው መሳሪያዎች ሳይታገዝ፣ በየጊዜው የአፈሩ ለምነት እየቀነሰ ከሄደው መሬትና ባህላዊ የአስተራረስ ዘዴ ጋር እየታገለ ቁጥሩ እየናረ የሚሄደውን ህብረተሰብ ከመመገብ ወደ ኋላ ብሎ አያውቅም። ግብርናው ከቀደሙት ጊዜያት በተለየ ሁኔታ ትኩረት ባገኘበት በዚህ ዘመንም ከተደቀኑበት እጅ ጠምዛዥ ጉዳዮች ጋር ግብግብ ውስጥ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ ድርቅ፣ የፖለቲካና የገበያ አለመረጋጋት፣ የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ውስንነት፣ የተፈጥሮ አደጋ፣ የዘርፉ ኢንቨስትመንት አለመዳበር የዘርፉ ተግዳሮት ሆነው ቀጥለዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በ78ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ባደረጉት ንግግር በተለይ የአየር ንብረት ለውጥን ተጽእኖ በሚገባ አመላክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ በተለይ በአፍሪካና በሌሎች በማደግ ላይ ያሉ አገራት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ቀውስ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ እንዲበጅ እየሰራች መሆኗን ተናግረዋል። በተለይ ኢትዮጵያዊያን ከጫፍ ጫፍ እየተሳተፉበት ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የዚህ ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ላለፉት ተከታታይ አራት ዓመታት በሰራችው ስራ በአካባቢ ጥበቃና በግብርናው ዘርፍም ውጤት ማግኘቷ እሙን ነው። ነገር ግን ፈተናዎቹን በድል ለመሻገር የሚደረጉ ጥረቶችና በዘርፉ የተገኙ አበረታች ውጤቶች እንደተጠበቁ ሆነው አሁንም ዘርፉን በሰለጠነ የሰው ሃይል፣ በተደራጀ የግብርና መሳሪያና ማቀነባበሪያ በመደገፍ አገርና ህዝብ ከግብርናው ዘርፍ ማግኘት ያለባቸውን ጥቅም እንዲያገኙ ለማስቻል ብዙ መስራት ይጠይቃል። በተለይ የግብርና ሜካናይዜሽንን ከማስፋፋትና ዘመናዊ የግብርና ግብዓቶችን በበቂ ሁኔታ ከማቅረብ አኳያ መንግስት እየሰጠ ያለው ትኩረት የበለጠ መጠናከርና ማደግ ይኖርበታል። የግብርናና የገጠር ልማት የፋይናንስና ብድር አቅርቦትን ማጠናከር እንዲሁም የአካባቢና ስነ ምህዳር ጥበቃ ስራዎችን በዘላቂነት መተግበር ያሻል። በተለይ ኢትዮጵያ በልዩ ትኩረት እየሰራችበት ያለውን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ጉዳይ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብርና አሰራር በመቀየርና አማራጮችን በማማተር እውን ማድረግ ይጠይቃል። ኢትዮጵያ በዝናብ ወይም በመስኖ መልማት የሚችል ያልተነካ ሰፊ መሬት እንዳላት የሚታወቅ ሲሆን ይህን ያልታረሰ መሬት በአግባቡ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ አንዱ አማራጭ ነው። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ግብርናው ከ34 በመቶ በላይ የጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት ድርሻ ይዟል፡፡ በተጨማሪም ዘርፉ 79 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች መተዳደሪያ ሲሆን በተመሳሳይ 79 በመቶ የሚሆነውን የውጭ ንግድ ገቢ በመሸፈንና ለአገር ውስጥ ኢንቨስትመንትና ገበያ የጥሬ እቃ አቅራቢ በመሆንም ይታወቃል። መንግስት በግብርናው ዘርፍ የወሰዳቸው የሪፎርም ስራዎችና ግብርናን ከአረንጓዴ አሻራ ጋር በማስተሳሰር የሰራቸው ስራዎች ፍሬ ማፍራት ጀምረዋል። በተለይ የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የተሰራው ስራ ቀዳሚ ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ብቻ የስንዴ ምርታማነቷን በ27 በመቶ ማሳደግ መቻሏ ስንዴ ከመሸመት ወደ መላክ የመሸጋገሯ ማረጋገጫ ሆኗል። በጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ አህመድ የተጀመረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በዚህ ረገድ የሚታይ ለውጥ እያሳየ ሲሆን በተሰራው ውጤታማ ስራ ባለፈው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ከውጭ ስንዴ አላስገባችም። በዚህም 1 ቢሊዮን ዶላር ማዳን መቻሏን የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ በቅርቡ ማሳወቃቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት 15 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቶን ስንዴ ያመረተች ሲሆን በተያዘው ዓመት ደግሞ ምርቱን ወደ 19 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቶን ለማሳደግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል። ይህንኑ ግብ ለማሳካት ደግሞ የስንዴ ማሳዋን በማሳደግ 5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል ለመሸፈን እየሰራች ነው። ከዚህ ውስጥ በመስኖ የሚለማ ስንዴን በ2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ በመዝራት በመስኖ የሚለማውን ስንዴ በ54 በመቶ ለማሳደግ እየሰራች ነው። ይህ ደግሞ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርቱን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እንደሚያስችል ዶክተር ግርማ አመንቴ ተናግረዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ያወጣው ሪፖርት እንደሚያመላክተው የግብርናው ዘርፍ በአስር ዓመቱ የልማት ዕቅድ የመጀመሪያዎቹ 3 ዓመታት (2013-2015) በዋና ዋና ተግባራት ከዕቅድ በላይ ዕድገት አስመዝግቧል። በዚህም ዘርፉ በ2013 ከነበረበት 5 ነጥብ 1 በመቶ በ2014 ወደ 5 ነጥብ 8 በመቶ ያደገ ሲሆን በ2015 ደግሞ 6 ነጥብ 3 በመቶ እድገት አስመዝግቧል። ግብርናውን ለማሳደግ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው የሰብል ምርት ሲሆን ለዘርፉ ማደግ 65 ነጥብ 5 በመቶ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ደን ልማት 8 ነጥብ 6 በመቶ እንዲሁም የእንሰሳት ሃብት ልማቱ 25 ነጥብ 9 በመቶ ድርሻ ይዘዋል። በ2015 ዓ.ም ጠቅላላ 627 ሚሊዮን ኩንታል ሰብል ለማምረት ታቅዶ ከተቀመጠው ግብ በላቀ ደረጃ 639 ሚሊየን ኩንታል ምርት ማግኘት ተችሏል። ከበጋ ስንዴ ልማት ጎን ለጎን በቅርብ ጊዜ የተጀመሩ የቡና፣ አቮካዶና አኩሪ አተር የመሳሳሉት ትላልቅ የግብርና ልማት ስራዎች በተመሳሳይ ውጤት ታይቶባቸዋል። የአዝርት፣ የአትክልት፣ ፍራፍሬና ስራስር ምርት ከፍተኛ የዕድገት ሽግግር የታየባቸው ናቸው። በአረንጓዴ አሻራ፣ በሌማት ትሩፋትና በከተማ ግብርና ተሞክሮ ሊወሰድበት የሚችል አፈጻጸም መመዝገቡ በሪፖርቱ ተመላክቷል። ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን የስንዴ ምርት ከውጭ ገበያ ስትገዛ የኖረች ሲሆን በተለይም በተለያዩ ጊዜያት የሚፈጠሩ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች አቅርቦቱን ሲያስተጓጉሉት ቆይተዋል። አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ የስንዴና የገብስ ምርትን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት የቻለች ሲሆን የሩዝ ፍላጎቷን ደግሞ 50 በመቶ መሸፈን ችላለች። በስንዴ ምርታማነት የተገኘውን ተሞክሮ ወደሌሎች ሰብሎች በማስፋት የገቢ ምርቶችን በቀጣይ ለመተካት በትኩረት እየተሰራበት ይገኛል። ይህንን ለማሳካት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ እንደሚሆን ይታመናል። በተለይ ለግብርና ዘርፉ የተሻለ በጀት መመደቡ፣ እስካሁን ለመጣውና ለወደፊትም ይመጣሉ ተብለው ለሚታሰቡ ለውጦች ትልቅ ምክንያት ነው። ለምሳሌ የ2015 ዓ.ም. በአገሪቱ ለተለያዩ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልማት ከተመደበው 786 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በጀት ውስጥ፣ ለግብርናው ዘርፍ 34 በመቶ የሚሆን በጀት ተመድቧል። ይህ ደግም ከለውጡ በፊት ከአሥር በመቶ ያልበለጠ በጀት ጋር ሲነፃፀር እጅግ ከፍተኛ ያደርገዋል። በተጨማሪም መንግሥት ለኩታ ገጠምና ለመስኖ እርሻ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱ፣ ሙሉ በሙሉ በዝናብ ላይ ጥገኛ የሆነውን የግብርና ስራ በመስኖ የታገዘ እንዲሆንና አርሶ/አርብቶ አደሩ በዓመት ከአንድ ጊዜ በላይ እንዲያመርት ማድረጉ ውጤቱን ጉልህ አድርጎታል። እንደ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ሩዝ፣ ቡና፣ አቦካዶ ሁሉ በግብርና ሚኒስቴር ከተያዙና በልዩ ትኩረት ከሚከናወኑ ዕቅዶች አንዱ የማር ምርትን ማሳደግ ሲሆን፣ በአሥር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ እንደተመላከተውም የማር ምርትን በማዘመን ምርቱን ለማሳደግ በስፋት ይሰራል። በኢትዮጵያ ለማር ምርት ተስማሚ የሆነ አግሮ ኢኮሎጂና ብዛት ያላቸው ዕፅዋት መኖራቸው የሚመረተው ማር የተፈጥሮ ጥራት እንዲኖረው ያግዛል። ይህንኑ ዕምቅ ሀብት ትኩረት ሰጥቶ ማልማት ከተቻለ ከ500 ሺሕ ቶን በላይ ማርና ከ50 ሺሕ ቶን በላይ ሰም ማምረት እንደሚቻል ባለሙያዎች ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እንስሳት ሀብት ኢንስቲትዩት ባወጣው መረጃ በሀገሪቱ አለ ተብሎ ከሚገመተው ሰባት ሚሊዮን የንብ መንጋ ውስጥ 90 በመቶው በባህላዊ ቀፎ ውስጥ የሚገኝ ነው። የንብ መንጋዎቹ በባህላዊ ቀፎ ከመኖራቸው በተጨማሪ በጫካ መገኘታቸው ሃብቱ ለአገር ዕድገት በሚፈለገው ልክ እንዳይውል አድርጎታል። ያም ቢሆን ባለፈው ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተጀመረው “የሌማት ትሩፋት” ለማር ምርት ትኩረት የሰጠ በመሆኑ ዘመናዊ የንብ ማነብ ዘዴ እንዲስፋፋ ተደርጓል። በዚህም የማር ምርታማነትን በዓመት ወደ 98 ሺህ ቶን ማሳደግ መቻሉ በቅርቡ መገለጹ ይታወሳል። ምርቱን በእጥፍ ለማሳደግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑም እንዲሁ። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የማር ምርት የማምረት አቅም ካላቸው አሥር ሀገሮች አንዷ በመሆኗ ሃብቱን ለማልማት ሁሉም ሊረባረብ ይገባል። በአጠቃላይ መንግሥት ለአረንጓዴ ልማት/አሻራ፣ ለአፈርና አካባቢ ጥበቃ የሰጠው ትኩረት ሁሉን አቀፍ የግብርና ዕድገት እንዲመጣ መሠረት ሆኗል። በተጨማሪም መንግስት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሌማት ትሩፋትና ምግባችን ከደጃችን መርሐ ግብር ኅብረተሰቡ የከተማ ግብርናን እንዲያስፋፉ በገጠርም ሆነ በከተማ ያከናወነው ተግባር ውጤት አስመዝግቧል። በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት ዘርፉን ለማዘመን የተከናወኑ የልማትና የሪፎረም ሥራዎች ግብርናውን ከአዝጋሚ ጉዞ በማውጣት ወደ ፈጣንና አስተማማኝ ጉዞ ማሸጋገር ችለዋል። ኢትዮጵያ አሁንም አያሌ ያልተነኩ ዕምቅ ሀብቶች ያሏት መሆኗን እንደ እድል በመውሰድ ቀጣይነት ያለው እድገት ማስመዝገብ ይጠበቅባታል። ይህን ማድረግ ስትችል የግብርና ሽግግር ይረጋገጣል። ግብርናውን ለማሻገር ደግሞ በፋይናንስ፣ በግብአት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሰለጠነ የሰው ሀይል ልማት ላይ በትኩረት መስራት ያሻል። ወጣቱ ግብርናን እንደ ንግድ (Agri-Bussiness) ማየትና በዚያው ልክ መስራት ይጠበቅበታል። በዚህ ልክ በርብርብ ሲሰራ ግብርናን በማሸጋገር ገበታን ከመሙላት ወይም ከፍጆታ አልፎ ገበያን ማማተር ይቻላል።
ኢትዮጵያ እና መስከረም
Sep 22, 2023 638
(በአየለ ያረጋል) መቼስ ሀገሬው መስከረምን ሲናፍቅ ‘ለብቻ’ ነው። በባህሉ፣ በትውፊቱ፣ በስለ-ምኑ፣ በኪነ-ቃሉ እና ስነ-ቃሉ ልዩ ሥፍራ ይሰጠዋል ለመስከረም። እንደ መስከረም ክብር፣ ሞገስ እና ፀጋ የተቸረው የትኛው ወር ይሆን? ማንም! ሀገሬው ለቆንጆ ልጁ ስም ሲያወጣ ‘መስከረም’ እንጂ በሌላ ወር ሰይሞ ያውቃል? አያውቅም። በኢትዮጵያ ምድር መስከረም ለሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን ለእንስሳት እና አዕዋፋት ራሱ ልዩ ጊዜ ነው። ‘ኢትዮጵያ ነይ በመስከረም…’ እንዲሉ መስከረም ለኢትዮጵያ ውበቷ፣ ቀለሟ፣ ትዕምርቷ፣ የባህር ሃሳቧ መባቻ ነው። ተናፋቂው መስከረም ዝም ብሎ ወር ብቻ አይመስልም። እውቁ ሠዓሊ እና ባለቅኔ ገብረክርስቶስ ደስታ መስከረምን “… በሽቱ መዓዛህ ለውጠው ዓመቱን፤ ይታደስ ያረጀው ፍጥረት ሌላ ይሁን…” ሲል የአዲስ ተስፋና መንፈስ መሻቱን አሳይቷል። ተወዳጇ ድምፃዊት እጅጋየሁ ሽባባው ደግሞ “… መስከረም ለምለሙ፣ መስከረም ለምለሙ፣ ብሩህ ዕንቁጣጣሽ ደስታ ለዓለሙ…” ትለዋለች መስከረምን ስታዜመው። እንደየ ንፍቀ ክበቡ ዓመታት በወራት ሲመነዘሩ የራሳቸው መልክና መገለጫ አላቸው። ኢትዮጵያም ከጎርጎሮሳዊያኑ የዘመን ቀመር በሰባት ዓመት ከስምንት ወራት ልዩነት ያለው የራሷ የዘመን ቀመር አላት። ኢትዮጵያ ብቸኛዋ ባለ 13 ወራት ሀገር ነች። ወራቱም መጸው(መኸር)፣ ሐጋይ(በጋ)፣ ፀደይ(በልግ) እና ክረምት በሚል በአራት ወቅቶች ይከፈላሉ። ወቅቶቹም የራሳቸው ጸባይ፣ ክዋኔ፣ ትውስታና ትዕምርት ይቸራቸዋል። እያንዳንዱ ወርም እንደዚሁ። ከዘመን መባቻው መስከረም እስከ ማዕዶተ-ዘመኗ ጳጉሜን ወራቱ በሰማይና በምድሩ ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ውቅራቸው ግላዊ ገጽታ ይነበብባቸዋል። የወራቱ ቅላሜ እና ሕብርነት ልዩ መልክዓ-ኢትዮጵያን ይፈጥራል። ‘የ13 ወር ፀጋ’ የሚለው መጠሪያም በ‘ምድረ ቀድምት’ እስኪተካ ድረስ ለብዙ አሥርት ዓመታት መለያ ሆኖ ዘልቋል። ይህን መለያ ስም ያወጡት እና የኢትዮጵያ ቱሪዝም አባት የሚሰኙት አቶ ኃብተሥላሴ ታፈሠ “ኢትዮጵያ የ13 ወራት ፀሐይ ባለቤት ናት። ስያሜው ከምንም የፖለቲካና ሃይማኖት ጋር ንክኪ የለውም” ብለው ነበር። የኢትዮጵያ ወራት ስያሜ ከመልክና ግብራቸው ይመነጫል። የወራት መባቻው መስከረም እንደዛው። ሊቃውንት መስከረምን ሲፈትቱት መስ - 'ዐለፈ፤ ከረመ' ይሉትና “ክረምቱን ማስከረሚያ፤ የጥቢ መባቻ" ወርኅ ሲሉ ያመሰጥሩታል። መስከረም ዘመን ያስረጃል፤ አዲስ ሕይወትና ተስፋ ደግሞ ይደግሳል። አንዳንዴም ይህ ወር ዘመን መለወጫ፣ ዕንቁጣጣሽ፣ ቅዱስ ዮሐንስ ተብሎም ይጠራል፡፡ 'አገር፣ ቀለም፣ ዘመን' እንደሸማው በድርና ማግነት ከሚሰባረቅባቸው ወራት አንዱ መስከረም ነው። መስከረም አገርኛ አለባበስ፣ አገርኛ ዝማሬ፣ አገርኛ ጨዋታ፣ አገርኛ ትውፊትና ቀለም በመስከረም በዓላት በተግባር ይታያል። መስከረም ሁለንተናዊ ውበቱ ድንቅ ነው፤ ትዕምርቱም ጉልህ ነው። የመልክዓ-መስከረም ድምቀት ማሳያዎች ዘመን መለወጫ በኢትዮጵያ ዘመን ስሌት ቀለበት መስከረም 1 ቀን ዘመን ይለወጣልና። የዘመን መለወጫ በዓል ‘ርዕሰ ዓውደ- ዓመት’ ይሰኛል። የባህር ሐሳብ ሊቃውንት መስከረም ለምን የዘመን መለወጫ እንደሆነ ሲያትቱ “ብርሃናት /ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት/ የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው” ይላሉ። በመስከረም ሌሊቱ ከቀኑ እኩል ነው። ደራሲ ካሕሳይ ገብረእግዚአብሔር “ቀዳማይ፣ ርዕሰ ክራሞት፣ መቅድመ አውርኅ፣ ርዕሰ ዐውደ-ዓመት፣ የክረምት ጫፍ መካተቻ፣ የመፀው መባቻ” ይሉታል ወርኃ መስከረምን። እናም ዘመነ ማዕዶቷን፤ ወርኅ ተውሳኳን ‘ጳጉሜን’ ተሻግሮ መስከረምን መሳም ይጓ'ጓ'ል። የመስከረም ጥባት በአያሌው ይሻታል። 'መስከረም ሲጠባ ወደ አገሬ ልግባ …’ እንዲሉ የተሰደዱት በአዲስ ዓመት መባቻ የአገራቸውን አፈር ለመሳም ያማትራሉ። ’አበባዬ ሆይ፤ አበባዬ ሆይ’ የሚሉ ሕፃናት ተስፋና ምኞታቸውን በወረቀት ያቀልማሉ፤ የአበባ ስዕላት ይዘው በየደጃፉ ይሯሯጣሉ፤ የ’ዕደጉ’ ምርቃት ያገኛሉ፤ በደስታ ይንቦጫረቃሉ። በዚህ ድባብ ነው እንግዲህ መስከረምን የግዑዛንም የሕይወታውያንም የነፃነት፣ የተስፋና የፍቅር ወርኅ ተደርጎ የሚናፈቀው። የብዙ ሺህ ዘመናት ባለታሪኳ ኢትዮጵያ ተፈጥሯዊ አዱኛ ሳይርቃት በእርስ በርስ ጦርነት፣ በጠላት ፍላፃዎች እና በድንቁርና ብዛት... ሰንኮፎቿ ሳይነቀሉ በመልከ-ብዙ ምስቅልቅሎሽ ውስጥ ዛሬ ደርሳለች። ጊዜው የኢትዮጵያን መስከረም ያስናፍቃል። ዕንቁጣጣሽ መስከረም በአደይ አበባ የሚያሸበርቅ ወር ነው። የነገረ-ዕንቁጣጣሽ የትመጣ መልከ-ብዙ አተያዮች ይጠቀሳሉ። ለምሳሌ “ዕንቁ – ዕፅ አመጣሽ” ብሎ የአበባ መፈንዳት ለማመላከት እንደሆነ የሚጠቅሱ አሉ። ንግሥት ሳባ /አዜብ/ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን የእጅ መንሻ ይዛ ስትሄድ ንጉሡም “ዕንቁ ለጣትሽ ጌጥ ይሁንሽ” በሚል ቀንና ከሌሊት የሚያበራ ቀለበት ስለሰጣት ነው የሚል አፈታሪክም ይነገራል። የስያሜው መነሻ ያም ሆነ ይህ መስከረም ለመልክዓ-ምድሩ፣ ለሰውና ለእንስሳት ሁሉ ‘ፍስሐ ወተድላ’ የሆነ ወር ነው። በመስከረም ምድር በዕንቁጣጣሽ ትፈካለች፤ በአበቦች ታጌጣለች፤ ውኆች ይጠራሉ። ሰማዩም የክብረ-ሰማይ ብርሃኑን ያጎላል። ጥቁር ደመና ጋቢ ይገፈፋል፤ ክዋክብት እንደፈንዲሻ በዲበ-ሰማይ ይደምቃሉ። ዕጽዋትና አዝዕርት እንቡጦች ይፈነዳሉ። የመብረቅ ነጎድጓድ ተወግዶ የሰላምና የሲሳይ ዝናብ ይዘንባል። እንስሳት የጠራ ውሃ እየጠጡ፣ ለምለም ሳር እየነቸረፉ ይቦርቃሉ። እርሻ የከረሙ በሬዎች፣ ጭነት የከረሙ አህዮች መስከረም አንጻራዊ የእፎይታ ወራቸው ነው። ነጎድጓድ በአዕዋፋት ዝማሬ ይተካል። ንቦች አበባ ይቀስማሉ፤ ቀፏቸውን ያደራሉ። ቢራቢሮ ሳትቀር ‘በመስከረም ብራ ከኔ በላይ ላሳር..’ ብላ ትከንፋለች። በ’ዕንቁጣጣሽ’ ምድር ብቻ አይደለችም የምትዋበው። መስከረም ለሰው ልጆችም በተለይም ለወጣቶች የፍቅር፣ የእሸት እና የአበባ ወር ነው። የሰላም፣ የንጹህ አየር፣ የጤና ድባብ ያረብባል። የጋመ በቆሎ እሸት ጥብስ፤ ቅቤ ልውስ፤ ቅቤ በረካ ይናፈቃል። የተጠፋፋ ዘመድ አዝማድ ይገናኛል። ‘ሰኔ መጣና ነጣጠለን’ ብለው ወርኃ ሰኔን የረገሙ ተማሪዎች ተናፋቂያቸውን ያገኛሉና ‘መስከረም ለምለም’ ብለው ያሞካሹታል። የገበሬው የሰብል ቡቃያ ያብባል፤ እሸት ያሽታል። ጉዝጓዝ ሣር፣ ትኩስ ቡና ይሽታል። ደመራ ወመስቀል ሊቃውንት የደመራን የትመጣን ሲፈትቱ ‘ደመረ፣ ተሰባሰበ’ ይሉታል። ጎረቤት፣ የሩቅ የቅርብ ዘመድ አዝማድ ተደምሮ የሚከውነው ነውና። ነገረ መስቀሉ እምነቱ፣ ባህሉ፣ ትውፊቱ ብዙ ነው። መስቀል በሃይማኖተ-አበው ሀተታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን፣ ለፍጡር የሰው ልጆች ያለውን ጥልቅ ፍቅር የገለጸበት ዓርማ ነው። በዚህም መስቀልን አማኝ ምዕመናን እና ካህናት የደኅንነትና የእምነት ምልክታቸው፤ የርኩስ መንፈስ ማባረሪያ መሳሪያቸው አድርገው ይመለከቱታል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መስከረም 10 ቀን ‘ተቀጸል ጽጌ’ በሚል የክርስቶት መስቀል ግማድ (ቀኝ እጁ ያረፈበት ክፋይ) ከኢየሩሳሌም ተነስቶ ኢትዮጵያ የገባበትን ቀን ታከብረዋለች፤ መስከረም 17 ቀን ደግሞ መስቀሉ የተገኘበትን። መስከረም 16 እና 17 ቀን የሚከበረው የደመራ መስቀል በዓል ከሃይማኖታዊ አስተምህሮው ባለፈ ባህላዊ ትውፊትነቱ የጎላ በመሆኑ በአብዛኛው ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ይናፈቃል። ደመራና መስቀል የአንድነት፣ የፍቅር፣ የይቅርታ፣ አብሮነት፣ የምስጋና፣ የተስፋ… እሴቶች የሚገለጹበት ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ክብረ-በዓል ነው። ደመራ እና መስቀል በዓላት ሃይማኖታዊ የአደባባይ በዓል ቢሆንም እንደየ አካባቢው ባህል፣ መንፈሳዊነት፣ ትውፊት፣ ዕውቀት አገርኛ ህብር ጥበባት የሚጎሉበት፣ አገር የውበት አክሊል የምትደፋበት ዕለት ነው። መስቀል የዓለማችን የማይዳሰስ የኢትዮጵያ ወካይ ቅርስ መዝገብ ሥር ሰፍሯል። በመስቀል አገርኛ ቀለም ይጎላል። 'አገር፣ ቀለም፣ ዘመን' እንደሸማው በድርና ማግነት ይሰባረቃሉ። የባህር ማዶ ጎብኚዎች በአግራሞትና መደነቅ ሲናገሩ ይደመጣሉ። የዕንቁጣጣሽ ተከታይ የመስከረም መልክ ነው መስቀል። የደመራ አደማመር እና ማብራት ሥነ-ሥርዓት በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ተመሳሳይ እንዳልሆነ ደራሲ ካሕሳይ ገብረእግዚአብሔር ይተርካሉ። በትግራይ፣ በጎንደር፣ በወሎ፣ በዋግኸምራ፣ በአዊና በከፊል ጎጃም ደመራ ማታ ላይ ተደምሮ ንጋት ላይ ይለኮሳል። በከፊል ጎጃም፣ በሸዋ፣ በአዲስ አበባ፣ በጉራጌ፣ በጋሞ፣ በወላይታና ሌሎች የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ደግሞ እንደየ አካባቢው ተለምዶ መስከረም 16 ከእኩለ ቀን ጀምሮ እስከ አመሻሽ ድረስ ደመራው ይለኮሳል። መስቀል በአንዳንድ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ርዕሰ ዓውደ-ዓመት ይመስላል። በደቡብ ኢትዮጵያ መስቀል ከሃይማኖታዊ ይዘቱ ባህላዊ ጎኑ ይጎላል። ጉራጌዎች፣ ጋሞዎችና ሌሎችም መስቀልን ከሁሉም በዓላት የበለጠ ይናፍቁታል። የተራራቁ ቤተሰቦች የሚገናኙበት የፍቅር፣ የደስታና የእርቅ በዓል ነው መስቀል። በጋሞ ብሔረሰብ ባህል በዋዜማው ሰው ቢሞት እንኳን በሌሊት ተወስዶ ይቀበራል እንጂ ለቅሶ እንደማይለቀስ ይነገራል፤ ለሰው ብቻ ሳይሆን ለእንስሳቱም ልዩ መኖ እንደሚቀርብላቸው ይነገራል። ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ እንደሚባለው በጋሞዎች ደግሞ ‘ለመስቀል ያልሆነ ዱንጉዛ ይበጣጠስ’ በሚመስል መልኩ የባህል ልብስ አለባበስ እንደሚዘወተር መምህር ካሕሳይ (በሕብረ-ብዕር ድርሰታቸው) ጽፈዋል። መስቀል በጉራጌዎች ዘንድ እንደ አውራው በዓል ይቆጠራል። ለመስቀል ዓመቱን ሙሉ ዝግጅት ይደረጋል። አባወራው ሰንጋ ለመግዛት፣ እማወራ ማጣፈጫውን ለማዘጋጀት፣ ወጣቶች ደመራና ደቦት ለማዘጋጀት፣ ልጆች ምርቃት ለመቀበል የየራሳቸውን ይዘጋጃሉ። ቤተሰብ ወዳጅ ዘመድ የሚጠያየቅበት፣ ለትዳር የደረሱ ሚስት የሚያጩበትና የሚመርጡበት ጥላቻና ቂም በፍቅርና በይቅርታ የሚታደስበት ነው። በጉራጌዎች ዘንድ መስቀል ትልቅ ቦታ ይቸረዋል። መስቀል እንደየአካባቢውና ባህሉ የሚናፈቅበት ዕልፍ ገጽታዎች አሉት። ለምሳሌ እኔ በተወለድኩበት ገጠራማ አካባቢ ያለውን በወፍ በረር እንቃኘው! በደመራ ዋዜማ ቀናት ልጆች ተራራ ለተራራ፣ ወንዝ ለወንዝ፣ ቋጥኝ ለቋጥኝ በልጅነት ወኔና ስስት በመዞር ለደመራ የሚሆን እንጨት፣ አደይ አበባ፣ ደቦት(ችቦ) ያጠራቅማሉ። ልክ መስከረም 16 አመሻሽ ከብቶች ወደ ግርግም ከገቡ የመንደሩ ወጣቶች ወደ ‘አፋፍ’ ይወጣሉ። ደመራ ወደሚደመርባት ሥፍራ። ሁሉም የአንድ ዕድር አባላት ቤተሰብ ተወካዮች ባሉበት እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት የደመራው ሥራ ይጠናቀቃል። ደመራው ሲጠናቀቅ ወደየ ቤታችን እንበታተናለን። (አዲስ አበባን ጨምሮ በከተሞች እንደሚደረገው በመስከረም 16 አመሻሽ ደመራው አይለኮስም። ይልቁኑ መስከረም 16 ለ17 አጥቢያ ጀምሮ ይለኮሳል እንጂ።) ለመስከረም 17 አጥቢያ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ ሁሉም ሰው ከየቤቱ ደቦቱ (ችቦውን) እየለኮሰ ‘እዮሃ ደመራ’ እያለ ወደ ደመራው ሥፍራ ይተማል። እንደየ ግለሰቡ ቤት እስከ ሦስት ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ሊጠይቅ ይችላል። የመስከረም እኩሌታ አረንጓዴያማ ውብ ማሳ ከየቤቱ ከሚወጡ የችቦ እሳት ነበልባል ብርሃን ይታጀባል። ከሌሎች አጎራባች የመንደር ደመራዎች ቀድሞ ለመለኮስ ጉጉቱ የትየለሌ ነው። ከቤት እስከ ደመራው ሥፍራ እስኪደርሱ ድረስ ሰዎችን፣ በረት ያሉ ከብቶቹንና የጓሮ አዝመራውን ጨምሮ ሕይወታዊያንን በሙሉ “እንጎረጎባህ፤ እንጎረጎባችሁ” ይባላል። የተጠያቂው ሰው ምላሽ ደግሞ “ዓመት ዓመቱን ያድርስህ” የሚል ይሆናል። ከደመራ ግጥም ተዘውታሪ ስንኞች መካከልም፡- “እዮሃ አበባዬ፣ መስከረም ጠባዬ፣ እዮሃ አረሬ አረሬ፣ መስቀል ጠባ ዛሬ፣ በሸዋ በትግሬ…” የሚለው ይጠቀሳል። ከደመራው ሥፍራ ስንደርስ የ’እንጎረጎባህ!’ ድምፆች ይበረታሉ። የ’ዓመቱን ያድርስህ’ መልስ ካልሆነም እኩይ አፀፋ ይኖራል። ሁሉም ከተሰባሰበ በኋላ ደመራን የሚያሞካሹና የአዲሱን ዓመት መልካምነት የሚመኙ ‘እዮሃ አበባዬ” ግጥሞች እየተደረደሩ ደመራው ሦስት ጊዜ እንቧለሌ ይዞራል። በዕድሜ ታላቅ እና የተከበረ ሰው በቅድሚያ ደመራውን ይለኩሳል። ቀጥሎ ሁሉም ወደ ደቦቱን(ችቦውን) ወደ ደመራው ውስጥ ያስገባል። ደመራውም ይቀጣጠላል። የእሳቱ ነበልባል በመስከረም የንጋት ውርጭና ብርድ ላይ ያይላል። ሁሉም በደመራው ዙሪያ ተኮልኩሎ የክረምት ወራት ትዝታ ይነሳል፤ ሹፈት፣ ቀልድና ቁምነገር በየፈርጁ ይሰለቃል። ሌሊቱ የአህያ ሆድ እስኪመስል ይቀጥላል። የተጣላም ይታረቃል። የደመራው አምድ (ምሰሶ) አወዳደቅ ለማየት ሁሉም በጉጉት ይጠብቃል። ምሰሶው ወደ ምሥራቅ ከወደቀ የጥጋብ ዓመት፤ ወደ ምዕራብ ከሆነ ግን የችጋር ዓመት ተደርጎ ይታመናል። ከደመራው ሁነቶች አንዱ ባህሉ የበቆሎ እሸት ናፍቆት ነው። የደመራው ምሰሶ ከወደቀ በኋላ በአቅራቢያ ካለ የበቆሎ ማሳ በቆሎ እሸት ይመጣል። በመስቀል ደመራ ፍም ተጠብሶ ይበላል። ባለበቆሎው ሰው ዓመታዊ ደንብ ስለሆነ የበቆሎ ማሳዬ ተጎዳብኝ ብሎ አይቆጣም። ከደመራው ዓመድ ግንባራችን ላይ መስቀለኛ ምልክት ማድረግ እና ‘የዛሬ ዓመት አድርሰኝ’ ስለት ይቀጥላል። ሰማዩ የአህያ ሆድ ሲመስል ልጆች በደቦ ወደ መንደር ለመንደር በመዞር ‘እንጎረጎባችሁ’ እንላለን። የቤቱ ባለቤትም በሳህን፣ ጣሳ ወይም ሌላ ዕቃ ጤፍ ዱቄት ይሰጣል። የሰበሰብነውን ዱቄት ይዘን ወደ ደመራው ሥፍራ እንመለሳለን። በደመራው ጉባዔ ተወስኖ ከዕድሩ ለተመረጠች ቀጭን እመቤት (ባለሙያ ሴት) ዱቄት ይሰጣትና በ17 ምሽት ለሚኖረው የእራት ሰዓት ዝግጅት በአነባበሮ መልክ ዱቄት አብኩታና ጋግራ ታቀርባለች። መስቀል የወል ክብረ በዓል ነው። የመስቀል ዕለት (መስከረም 17) በግ ይታረዳል። እህል ውሃ ቀርቦ የመንደሩ ሰው በጋራ ሲጫወት ይውላል፤ በሕብረት ይበላል። ለመስቀል የተጣላ ጎረቤት ይታረቃል። ልጆች በሕብረት ይቦርቃሉ። የመስቀል ትዝታ በእኛ መንደር ይናፈቃል። ሁሉም እንደየ ቀየው ትውፊት እና ልማድ ይህን ሁነት ይናፍቃል….!! ጊፋታ ጊፋታ/ ግፋታ ማለት ትርጉሙ በኩር ወይም ታላቅ ማለት ሲሆን በለኬላ ትርጓሜው መሻገር ማለት ነው፡፡ በወላይታ ብሔረሰብ አዲስ ዓመት አንድ ብሎ የሚጀመርበት የአዲስ ዓመት መግቢያና የብርሃን ጊዜ ማብሰሪያ ነው፡፡ ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሻገር የሚለውንም ይገልጻል፡፡ ጊፋታ የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ስያሜ ነው፡፡ በወላይታ ብሔረሰብ ዘንድ መስከረም ወር በገባ ከቀን 14 እስከ 20 መካከል የሚውለው እሑድ አዲሱን ዓመት የሚቀበሉበር ዕለት ይሆናል፡፡ በዓሉ የሚውልበት እሑድ ስሙም ‹‹ሹሃ ወጋ›› የእርድ እሑድ ይባላል፡፡ እሑድ የአዲስ ቀን ብሥራትም ነው፡፡ ቀጣዮቹ የሳምንቱ ቀናት የየራሳቸው ስያሜና አከባበር አላቸው። ለአብነት ‹‹ጋዜ ኦሩዋ›› ማንሳት ይቻላል። የአዲስ ዓመት አራተኛ ቀን ነው። የሰፈሩ ወጣቶች በየመንደሩ በታዋቂ የአገር ሽማግሌዎች ደጅ ተሰባስበው የግፋታ በዓል ባህላዊ ጨዋታ የሆነውን ጋዜ በጋራ ሆነው ‹‹ሀያያ ሌኬ›› እያሉ ትከሻ ለትከሻ ተቃቅፈው የሚጫወቱበትና ልጃገረዶችን ሎሚ በመለመን የሚፈልጓትን የሚመርጡበት ጨዋታ የሚጫወቱበት ቀን ነው፡፡ በዕለቱ ልጃገረዶች አንድ ላይ ሆነው በየቡድን ቁጭ ብለው ወንዴና ሴቴን ከበሮ እየመቱ ‹‹ወላወላሎሜ›› እያሉ የሚመርጡትን ወንድ ሎሚ በመስጠት የሚመርጡበት፣ እንዲሁም ሴቶች ለሚዜነትና ለጓደኝነት ከመረጧት ሴት ጋር በጥርስ አንድ ሎሚን ለሁለት የሚከፋፈሉበትና ስማቸው ሲጠራሩ ‹‹ሎሜ ሎሜ›› የሚባባሉበት ጨዋታ የሚጫወቱበት ዕለት ጋዜ ኦሩዋ ነው፡፡ ግፋታ ሲሸኝ ጥቅምት በገባ በመጀመሪያው ሳምንት ማክሰኞ ሆኖ የሽኝት በሬ ታርዶ ከተበላ በኋላ ቶክ ጤላ የተባለውን ምሽት በችቦ ያባርራሉ፡፡ ዜማ በተቀላቀለበት ጩኸት ችቦ ይዘው ‹‹ኦሎ ጎሮ ባ! ሳሮ ባዳ ሳሮ ያ!›› ይላሉ፡፡ ትርጓሜውም ጊፋታ በሰላም ሄደሽ በሰላም ነይ! ማለት ነው፡፡ ዮ …ማስቃላ በጋሞዎች ዘንድ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀው «ዮ ማስቃላ» የዘመን መለወጫ በዓል በመስከረም ወር አጋማሽ ላይ ቅበላው ተከብሮ በዚሁ ወር መጨረሻ «ዮ ማስቃላ» ሽኝት በዓል በድጋሚ በድምቀት ይከበራል። መስከረም ወር የመጀመሪያው ቀን በጋሞ ዞን ”ሂንግጫ” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ይህም አዲሱን ዓመት ለመቀበል ዝግጅት የሚደረግበት ቀን ነው። ጋሞዎች ዓመቱን ሙሉ ገንዘብ በመቆጠብ በዓሉን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ይደረጋል። ወንዶች ለበዓሉ የሚሆን ሠንጋ መግዣ፣ ለልጆች ልብስ እና ጌጣጌጥ ማሟያ፤ እናቶች ደግሞ ለቅቤ፣ ለቅመማቅመም፣ ለባህላዊ ምግቦች እና መጠጦች እህል መግዣ የሚሆን ገንዘብ ያጠራቅማሉ። በጋሞ ዞን የማስቃላ በዓል ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለእንሳስት እና ለአዕዋፋትም ጭምር ነው ተብሎ ይታመናል፤ በዕለቱ ምግብ ከሰው አልፎ ለእንሳስት እና ለአዕዋፍም ይትረፈረፋል። ለከብቶችም የግጦሸ መሬት በየአካባቢው ይከለላል። በተለያዩ አጋጣሚዎች የተጣሉ ታርቀው፣ የተራራቁ ዘመድ አዝማድ እና ወዳጆች ተሰባስበው በዓሉን በጋራ እንዲያከብሩ ማድረግ የጋሞ ማስቃላ በዓል መገለጫ ነው። በጋሞ ብሔረሰብ የሚከበረው የማስቃላ በዓል በሶፌ ሥርዓት የታጀበ ነው። የቀደመው ዓመት ማስቃላ በዓል ከተከበረ በኃላ የተጋቡ ሙሽሮች ከመስከረም አጋማሽ ጀምሮ ማምሻውን በአደባባይ ከመላው ሕብረተሰብ ጋር የሚቀላቀሉበት እና ሁለቱም ተጋቢ ቤተሰቦች አንድ ላይ ሆነው ደስታቸውን የሚገልፁበት ሥርዓት ነው። የመጨረሻው የማስቃላ ሽኝት በዓል ነው፤ ይህ ሥርዓት እንደየአባወራው አቅም በፈቀደ መጠን የሚፈፀም ነው። በዚህ ዕለት ሁሉም ያለ ፆታ ልዩነት በአደባባይ ላይ ወጥተው ያኑረን እስከ ወዲያኛው እንኖራለን እያሉ ይጨፍራሉ። ከዚህ በኋላ ለመጪው ዓመት በሰላም በጤና ያድርሰን ተባብለው ፈጣሪን በመማፀን ዝግጅቱ ይቋጫል። ያሆዴ መስቀላ የክረምቱ ወራት አልፈው መስኩ በልምላሜና በአደይ አበባ ሲያሸበርቅ በሃድያዎች ዘንድ ትልቅ ዝግጅት አለ - ያሆዴ መስቀላ። “ያሆዴ“ ማለት እንደ ብሔሩ የባህል ሽማግሌዎች ትርጓሜ እንኳን ደስ አላችሁ፤ የሚል የብስራት ትርጉም ያለው ሲሆን ”መስቀላ” ማለት ደግሞ ብርሃን ፈነጠቀ ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ያሆዴ መስቃላ ብርሃን ፈነጠቀ እንኳን ደስ አላችሁ የሚል ትርጉም አለው። በዓሉ በወርኃ መስከረም 16 የሚከበር ሲሆን ወሩ ብርሃን፣ ብሩህ ተስፋ፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ረድኤት፣ በረከት የሚሞላበት ተምሳሌት ወር ተደርጎ ይቆጠራል። የሃድያ አባቶች ”ከባለቤቱ የከረመች ነፍስ በያሆዴ መስቀላ ትነግሳለች“ የሚል ብሂል አላቸው። የሃድያ አባቶች እንደ ዘመን መለወጫ የመጀመሪያ ቀን አድርገው በመውሰድ ማንኛውንም ዓይነት ክስተት ከዚያ ጋር አያይዘው እንደሚቆጥሩ ይነገራል። በዓሉ ከመድረሱ በፊት ሁሉም የቤተሰብ አባላት በዓሉን ለማድመቅ የየራሳቸው ድርሻ አላቸው። በብሔሩ አባቶች አብሮነታቸውን ከሚያጠናክሩባቸው ማኅበራዊ እሴቶች መካከል አንዱ ቱታ/ሼማታ/ሲሆን ይህ ማለት በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተደራጀ ቋሚ የሆነ ከአራት እስከ ስምንት አባላትን የያዘና በሥጋ ቅርጫ የተደራጀ ማኅበር ነው። የዚህ ማኅበር አባላት ግንኙነት ያላቸው የሚተሳሰቡ የኢኮኖሚ አቅማቸውም ተቀራራቢነት ያለው ሲሆን በመቀናጀት የበዓሉ እለት ከመድረሱ በፊት በጋራ ገንዘብ ማስቀመጥ ይጀምራሉ፤ በበዓሉ ወቅትም ለእርድ የሚሆን በሬ መግዣ ገንዘብ እንዳይቸገሩና በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ ሕብረታቸው ትልቅ ሚና ይጫወታል። ከመጋቢት ወር ጀምሮ ለከብቶች የግጦሽ ሳር የሚሆን ቦታ ከልሎ በማስቀመጥ የበዓሉ ቀን ከብቶች ተለቀውበት እንዲጠግቡ የሚደረግ ሲሆን በአዲስ ዓመት መግቢያ እንኳን የሰው ልጅ እንሰሳትም ቢሆኑ መጥገብ እንዳለባቸው እንዲሁም የጥጋብ ዘመን እንዲሆን በብሔሩ በዓሉ ለሰው ብቻ ሳይሆን እንሰሳትም ሆዳቸው ሳይጎድል አዲሱን ዓመት መቀበል እንዳለባቸው በመታመኑ ልዩ ትኩረት ይሰጣቸዋል። ኢሬቻ ኢሬቻ ከመስከረም ደማቅ መልኮች አንዱ ነው። ኢሬቻ የዘመነ መፀው መጀመሪያ ሁነት ነው። የኢሬቻ ክብረ በዓል ኢሬቻ ቢራ (መልካ) በሐይቆች ወይም በወንዞች ዳር የሚከበር ነው። ከክረምት ወደ መፀው መሸጋገርን ምክንያት በማድረግ የሚከወን የምስጋና በዓል ነው። በኦሮሞ ዘንድ ለዘመናት የሚከበር እና ከገዳ ሥርዓት ጋር የተቆራኘ እንደሆነ ይነገራል። ኢሬቻ ከመስቀል በኋላ ይከበራል። በቢሾፍቱ ከተማ የሚከበረው የ'ሆራ አርሰዲ' እንዲሁም ‘ሆራ ፊንፊኔ’ ከፍተኛ ሕዝብ ቁጥር በታደመበት በድምቀት ይከበራል። በሌሎችም የኦሮሚያ አካባቢዎች በተለያዩ ክዋኔዎች እንዲሁ ይከበራል። ኢሬቻ ለፈጣሪ (ዋቃ) የክረምት ወቅትን በማሳለፉ፣ ወይንም ወደ አዲስ ዓመት በማሸጋገሩ የሚቀርብ ምስጋና ነው። ‹‹ዋቃ›› ፍጥረተ ዓለምን ያስገኘውና ሒደቱንም የሚያስተናብረው አንድ አምላክ ማለት ነው፡፡ ‹‹ኢሬቻ ሰላም ነው፣ ሰላም ጥልቅ ትርጉም አለው፣ ሰው ከሰው ጋር፣ ሰው ከራሱ ጋር፣ ሰው ከተፈጥሮ ጋርና ሰው ከፈጣሪው ጋር ሰላም ሊኖረው ይገባል፤›› የሚለው ጽንሰ ሐሳብ የክብረ በዓሉ ጭብጥ ነው፡፡ ለሕዝቡና ለአገሩ ምርቃትና መልካም ምኞት የሚገለጽበትም ነው-ኢሬቻ። ታዲያ ማንኛውም ሰው ወደ በዓሉ ሥፍራ ሲሄድ አለባበሱን ማሳመር ይጠበቅበታልኢሬቻ ከመስቀል በኋላ ይከበራል። በቢሾፍቱ ከተማ የሚከበረው የ'ሆራ አርሰዲ' እንዲሁም ‘ሆራ ፊንፊኔ’ ከፍተኛ ሕዝብ ቁጥር በታደመበት በድምቀት ይከበራል። በሌሎችም የኦሮሚያ አካባቢዎች በተለያዩ ክዋኔዎች እንዲሁ ይከበራል። ኢሬቻ እንደ ዕንቁጣጣሽ በመስከረም ጥባት ውሃ ጎድሎ፣ የተራራቀ ዘመድ አዝማድ የሚገናኝበት ነው። በተለያዩ ጸሐፍት እንደተጠቀሰው፣ ኢሬቻ አንድም ‘ዋቃ’ ከብርድና መብረቅ፣ ከጎርፍ፣ ከአውሎ ነፋስ እና መሰል የክረምት ተፈጥሯዊ ክስተቶች ጠብቆ ወደ ብራ እና ፀሐያማው የመፀው ወቅት በሰላም ስላሸጋገረ፣ አንድም በዋቃ ፈቃድ ዝናብ ዘንቦ፣ መሬቱ ረስርሶ፣ አዝመራው ለምልሞ፣ መልካም ፍሬ በመታየቱ፣ እሸት በመስጠቱ ስለማያልቀው ቸርነቱ ለማመስገን ነው። ከክረምቱ ጨለማ ወደ ብርሃን የማለፍ ብሥራት ነው ኢሬቻ። በሌላ በኩል ደግሞ መጪው አዲሱ ዓመት የተባረከና የተቀደሰ፣ የደስታና የብልፅግና፣ የተድላና ፍስሃ ይሆን ዘንድ መልካም ምኞትን የመግለጫ በዓልም ነው። በኢሬቻ ክዋኔ አባ ገዳዎችና የሕዝብ መሪዎች ይመርቃሉ። በኦሮሞ ሕዝብ ባህላዊ አለባበሱን በማጌጥ ወደ ክብረ-በዓሉ የሚያመሩ ኢሬቻ አክባሪዎች እርጥብ ሳር እና አደይ አበባን ይይዛሉ። ከኢሬቻ ክብረ-በዓል የምርቃት ስንኞች መዘን እንሰናበት። “… ለምድራችን ሰላም ስጥ! ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!)
ያሆዴ- የአዲስ ተስፋና ልምላሜ ምልክት
Sep 22, 2023 772
(በማሙሽ ጋረደው ከሆሳዕና) ያሆዴ የሃድያ ብሔር የአዲስ ዘመን መሸጋገሪያ በዓል ነው። በዓሉ ሲከበር ቂምና ቁርሾ ተወግዶ ያለፈው ዓመት መልካምና በጎ ያልሆነ ሁኔታ ታይቶ ለቀጣይ ስኬት አዲስ ተስፋና ልምላሜ ሰንቆ የሚሻገሩበት በዓልም እንደሆነ ይነገራል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የሃድያ ዞን አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ አቶ ታምሬ ኤርሚያስ እንዳሉት ሃድያ የራሱ የሆነ የጊዜ አቆጣጠር ባህል፤ ልማድ፤ ወግና ስርዓት አለው። ለዚህም እንደ ማሳያ በብሔሩ ዘንድ በከፍተኛ ድምቀት የሚከበረውን የያሆዴ ክብረ በዓል ለአብነት ጠቅሰዋል። በዓሉ የአዲስ ተስፋና ልምላሜ ምልክት ተደርጎ እንደሚወሰድ የተገለጸ ሲሆን በተለይም የሚመጣው ዘመን የስኬት እንዲሆን እያንዳንዱ ካለፈው ዓመት ስኬትና ውድቀት ልምድ እየቀመረ ሃገር ሰላም እንዲሆን ተመራርቀው በደስታ እየተበላ፤ እየተጠጣ የሚከበር በዓል መሆኑንም ተናግረዋል። በብሔሩ ዘንድ ልዩ ቦታ የሚሰጠው የያሆዴ ክብረ በዓል አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበትም ነው። በዓሉ ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ በተለያዩ ክዋኔዎች የሚከበር ሲሆን በዓሉ መቅረቡን ታዳጊ ልጆች በተለያዩ ገላጭ በሆኑ ድርጊቶች እንደሚያበስሩ አቶ ታምሬ ተናግረዋል። በተለይም ታዳጊዎቹ ያሆዴ መድረሱን ለማብሰር ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ እስከ ጳጉሜ መጨረሻ ድረስ በብሔሩ አጠራር ገምባቡያ ወይም (ዋሽንት) በመጠቀም የተለያዩ ጥዑመ ዜማዎችን በማሰማት በዓሉ መቅረቡን ያበስራሉ። በሃድያ ብሔር ዘንድ የአዲስ ዘመን ብስራት “ያሆዴ" የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰድ በዓል መሆኑንም አመልክተዋል። ይህም የሆነበት ምክንያት በመስከረም ሰውና እንስሳ ከዶፍ ዝናብ፣ ከውርጭ፣ ከጤዛና ከጭቃ፣ ከጉም፤ ከጭጋግና ጽልመት ነጻ ይሆናሉ። ምድሩ በሃምራዊ ቀለም ደምቆ ያሸበርቃል። ፀሐይ ሙሉ ገላዋን ገልጣ ጸዳሏን ትሰጣለች። በመሆኑም በስራ የደከመ ሰውነት ዘና፣ የታመመ ቀና ይልበታል፣ ልጅ አዋቂ የደስታ ነጋሪቱን ይጎስማል፣ የፍቅር ጽዋ ይጠጣል፣ የአእምሮ እርካታ ይነግሳል፣ በሁሉም ነገር ደስታ ይሰፍናል ወርሃ መስከረም በጥጋብና ደስታ ይጀመራል ። በዓሉ ከመግባቱ በፊት የራሱ የሆነ የሥራ ክፍፍል ኖሮት ቅድመ ዝግጅት የሚደረግበት መሆኑን ያነሱት ሃላፊው የቤተሰብ አባላት ሁሉም በየድርሻቸው ሃላፊነታቸውን እየተወጡ እንደሚጠብቁት ተናግረዋል። ለአብነትም ለበዓሉ መድመቅ በዓሉ ከመድረሱ ሦስትና አራት ወራት በፊት በአንድ ቤት ውስጥ የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት የሚወጡት ድርሻ አላቸው። የሃድያ አባቶች የያሆዴን የዘመን መለወጫ በዓል የሚያከብሩት በቅንጅት አማካኝነት ከአራት እስከ ስድስት ሰው በመሆን ተቀናጅተው ሰንጋ በመግዛት ነው። ለበዓሉ ሰንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ ማስቀመጥ የሚጀምሩትም ቀደም ብለው ነው ። እናቶች በዓሉ ከመቃረቡ ከሦስትና እና አራት ወራት በፊት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ለማጠራቀም በሚገቡት (ዊጆ) በተሰኘ ዕቁብ ቅቤ ማከማቸት ይጀምራሉ። በተጨማሪም ለስጋ መብያና ለአተካና መስሪያ የሚሆን እንሰት በመለየትና በመፋቅ፣ ቆጮ፣ ሜሬሮና፣ ቡላን ጨምሮ የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት የድርሻቸውን ይወጣሉ። የደረሱ ልጃገረዶች የቤቱን ወለል ቆፍረው ይደለድላሉ፣ የተለያዩ ውበት የሚሠጡ ቀለማትንና የተለያዩ ኖራዎችን በመጠቀም የቤቱን የውስጥና የውጭ ግርግዳን በመቀባት ያስውባሉ። ወጣቶች ከነሐሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚመርጡላቸውን ዛፍ፣ ግንድ ቆርጠው ለምግብ ማብሰያና ለደመራ የሚሆን ችቦ የማዘጋጀት ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይቆያሉ። ከመስከረም መግቢያ ጀምሮ ያሉ የቅዳሜ ገበያዎች ስያሜ (መቻል ሜራ ) የእብድ ገበያ በመባል ይጠራሉ።እነዚህ የግብይት ቀናት ከዚህ ቀደም እንደነበሩ የግብይት ቀናት በተረጋጋ መንገድ የሚተገበሩ ባለመሆኑና በጠዋት ቆሞ በጊዜ የሚበተን ገበያ በመሆኑ (መቻል ሜራ) የእብድ ገቢያ የሚል ስያሜ አሰጥቶታል ነው ያሉት አባቶች ሰንጋ ገዝተው ለመብላት ባደራጁት (ቱታ) ቅንጃ አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ ወደ መቻል ሜራ (እብድ ገበያ) በመሔድ የሚፈልጉትን ሰንጋ ገዝተው ይመለሳሉ። ገንዘብ ያላስቀመጡና በወቅቱ ማግኘት የማይችሉ አባወራዎች በዓሉን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተደስተው እንዲያሳልፉ ሌላኛው አማራጭ (ሃባ) በመባል የሚታወቅና ምንም ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች ለበዓሉ የሚሆን ሰንጋ በብድር የሚወስዱበት በብሔሩ ተወላጆች ዘንድ የኖረ የመተጋገዝና የመተሳሰብ እሴት አንዱ ነው። የሚፈልጉትን ሰንጋ ከመረጡ በኋላ እህል በሚደርስበት በታህሳስና በጥር ለመክፈል በዱቤ ይወስዳሉ። የበሬ ነጋዴውም ያለ ማንገራገር ሰንጋውን በመስጠት ወቅቱ ሲደርስ ገንዘቡን ለመውሰድ ተስማምቶ ይሰጥና ወቅቱን ጠብቆ ገንዘቡን ይወስዳል። በትውስት ተወስዶ ገንዘብ ያልከፈለ አባወራ ለቀጣይ የዘመን መለወጫ አይደርስም ተብሎ በብሔሩ ዘንድ ስለሚታመን በተስማሙበት ወቅት ገንዘቡን የመስጠት ግዴታቸው የተጠበቀ ነው። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ የመምሪያው ባለሙያ አቶ ይዲድያ ተስፋሁን እንዳሉት በዓሉ ያለው ለሌለው አካፍሎ በጋራ የሚበላበትና ወደ አዲስ ዘመን በጠንካራ አብሮነት የሚሻገሩበት ነው። በመሆኑም የያሆዴ በዓል በዜጎች መካከል ጠንካራ አንድነትና አብሮነትን መሰረት ያደረጉ ዕሴቶች ያሉበት መሆኑን አንስተው ለትውልድ ግንባታ የሚሆኑ ዕሴቶችን አጎልብቶ መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል ። ለበዓሉ ዋዜማ ከሚዘጋጁ ሁነቶች መካከል አተካና ልዩ ቦታ የሚሰጠው ነው። አተካና በተለይም ለዚህ በዓል ከዚህ ባሻገር ለትልልቅ እንግዶች ከሚዘጋጁ ምግቦች መካከል አንዱ ነው። አተካና ከወተት፣ ከቅቤ፣ አይብና ቡላ የሚዘጋጅና በበዓሉ የምግብ ፍላጎትን የሚከፍት ተበልቶ የማይጠገብ በእናቶች የሚዘጋጅ ጣፋጭ ምግብ ነው። የበዓሉ ዋዜማ አተካን ሂሞ (የአተካና ምሽት) የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን በዓሉን ለማክበር ከሩቅም ከቅርብም የተሰበሰበ ቤተሰብና እንግዶች በናፍቆት የሚመገቡት ምግብ ነው። በዚሁ ዕለት በአካባቢው ትልቅ የሚባል አባወራ (አዛውንት) ቤት ችቦ (ሳቴ ) ተዘጋጅቶ ማምሻውን አባቶች ወይም የሃገር ሽማግሌዎች የማቀጣጠያ (ጦምቦራ) ደመራ ማቀጣጠያ ይዘው ይወጣሉ። ከዚያም የአካባቢው ማህበረሰብም የሃገር ባህል ልብስ ለብሰው እንዲሁም ወጣቶች ተሰብስበው ያሆዴ ይጨፍራሉ። የሃገር ሽማግሌዎች ይመርቃሉ፤ ከዚያም የተዘጋጀውን ችቦ በእሳት ለኩሰው ያበራሉ። ይህም አዲስ ዘመን መግባቱን ማብሰርና ዓመቱ የብርሃን ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞት የሚገለፅበት ነው። ደመራው ከተቀጣጠለ በኃላ ወጣቶች ያሆዴ (ኦሌ) ጭፈራ ሲጫወቱ ያነጋሉ። ይህ ጭፈራ ከያሆዴ በዓል ውጭ አይጨፈርም። ወጣት ደመቀ አባቴ የሆሳዕና ከተማ ነዋሪ ሲሆን ስለ በዓሉ አስተያየቱን ሲሰጥ ''በአባቶች ደመራው ከተቀጣጠለ በኃላ እኛ ወጣቶች ያሆዴ ....ያህዴ....ሆያ ሆ... /ኦሌ/ ጭፈራ እየተጫወትን እናነጋለን፤'' ይህ ጭፈራ ከያሆዴ በዓል ውጭ ስለማይጨፈር በዓሉን ቀን በጉጉት እንደሚጠብቁት ተናግሯል። ተራርቀው የቆየ ወዳጅ ዘመድ ተሰብስቦ ያለምንም ልዩነት ችግርም ካለ በዕርቅና ሰላምን በማውረድ የሚመጣው ዘመን የልምላሜና የስኬት እንዲሆን ተመራርቀው የሚለያዩበት በዓል በመሆኑ በተስፋ የሚጠብቁት እንደሆነ ነው ወጣቱ የሚናገረው። የበዓሉ እለት ለዕርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኃላ የባህል ሽማግሌዎች (ጋቢማ ) ሥርዓት ያከናውናሉ። ክዋኔውም የበሬውን ሻኛ በለጋ ቅቤና በሠርዶ ሳር በመቀባትና ወተት በማፍሰስ ይከናወናል። ይህም በሚከናወንበት ወቅትም ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሃገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን በማለት (ፋቴ) ዳግም ምርቃት ፈጽመው በሬው ይጣልና የዕርድ ሥርዓት ይካሔዳል። በዕለቱም ከታረደው ሥጋ ቅምሻ በጋራ ይበሉና ቀሪውን ለማህበሩ (ለቱታ) አባላት ክፍፍል ይፈፀማል። ከእርድ ሥርዓቱ በኃላ በማግስቱ ልጆች ወደ ወላጆቻቸው ዘራሮ የሚባል አበባ ይዘው እየጨፈሩ ያስማሉ -ይመረቃሉ የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባባላሉ፤ ከስጋውም ፣ከቦርዴውም ፣ ከአተካናውም የሚመገቡበት ክዋኔ (ሚክራ) በመባል ይታወቃል። ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ስጋና (ዘራሮ) አደይ አበባ ጭምር ይዘው የሚሔዱበት እንዲሁም ያላገቡ ወጣቶች ለትዳር የሚሆናቸውን አጋር የሚፈልጉበትና የሚያጩበት ባህልም ያለው ነው ያሆዴ ክብረ በዓል። ከእርድ ስነ ስርዓቱ በኋላ ከሶስት ሳምንታት እስከ ወር ለሚሆን ጊዜ የመጠያየቂያና የመረዳጃ ወቅት ይሆናል። የያሆዴ በዓል ያሉ ዕሴቶች ለህዝብ ትስስር፣ ጠንካራ የስራ ባህልና ዘላቂ ሰላም ግንባታ ያላቸውን ሚና ለማላቅ በልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደምገባ የሚያነሱት በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የህዝብ ግንኙነትና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የአቶ ዳንኤል ገዴ በዚህ ላይ በአከባቢው ያሉ የማህበረሰብ ልምዶችና ወጎች ለትውልድ እንዲሸጋገሩ መስራትና የሃገር በቀል ዕውቀትን ማጠናከር እንደምገበባ ተናግረዋል። በዚህ ረገድ የዋቸሞ ዩኒቨረሲቲ የሃድያን ብሔር የዘመን አቆጣጠር ታሪክ : ባህልና ቋንቋ እንዲሁም ሌሎች ዕሴቶች ተሰንደው እንዲቀመጡና ለማስተማሪያነት እንዲውሉ ለማስቻል በጥናትና ምርምርና የተደገፈ ስራ በመስራት ላይ መሆኑን አመላክተዋል። በተጨማሪም ባህሉ ይበልጥ እንዲታወቅና በዩኔስኮ ተመዝግቦ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚገባውን ጥቅም እንዲያመጣና ከቱሪዝም አንጻር ሚናውን እንዲጫወት ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የመኔ ሸድዬ ባሮ - የጠንካራ የስራ ባህል፣ የአብሮነትና የሰላም ተምሳሌት
Sep 20, 2023 1339
በሽመልስ ጌታነህ (ኢዜአ) የመኔ ሸድዬ ባሮ የካፈቾ ብሄር ከአሮጌው ዘመን ወደ አዲሱ የሚሸጋገሩበት፣ የአዲስ ዘመን ብስራትና የዘመን መለወጫ በዓል ነው። በዓሉ የጠንካራ የስራ ባህል፣ የአብሮነትና የሰላም ተምሳሌት በዓል እንደሆነ ይነገርለታል። በዚህም የካፋ ብሄር ለዘመናት የገነባውና ጠንካራ የስራ ባህል፤ ተፈጥሮን የመጠበቅና የመንከባከብ እንዲሁም ከተለያዩ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ጋር ተቻችሎና ተፈቃቅሮ የሚኖር ሲሆን ቱባ ዕሴቱ ዛሬም ላለው ትውልድ መሰረት መሆኑን ያምኑበታል። የተለያዩ የታሪክ ድርሳናት እንደሚያሳዩት ከሆነ የካፋ ህዝብ ጠንካራ ንጉሳዊ ሥርዓት የነበረው፤ የታሪክና የቱባ ባህል ባለቤትም ነው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የታሪክ ባለሙያና የሀገር ሽማግሌ አቶ አሰፋ ገብረማሪያም የካፈቾ ብሄር ዘመን መለወጫ በሃገሬው አጠራር ''የመኔ ሸድዬ ባሮ'' በዓል የካፋ ህዝብ ከሚያከብራቸው በርካታ በዓላት ውስጥ ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው መሆኑን አፅንኦት ሰጥተው ይናገራሉ። በዓሉ ያለውን ግዝፈት ሲያመለክቱ በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በውጭ ፀሐፍት ጭምር “ታላቁ በዓል ወይም (ግሬት ፌስቲቫል)” ተብሎ እንደሚጠራም ተናግረዋል። በዓሉ ታሪካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ዳራ ያለው ሲሆን ከጥንት ካፋ ንጉስ ጀምሮ በየአመቱ በድምቀት የሚከበር በዓል እንደሆነም ጠቁመዋል። የካፋ ህዝብ ከ14ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ከጎሳ መሪነት አንስቶ ጠንካራ የመንግስት መዋቅር የነበረው ታላቅ ህዝብ እንደሆነ ያነሱት አቶ አሰፋ፣ በዚህም በዓሉ በዘመኑ የነበሩ መንግስታት በዓል እንደነበረም አብራርተዋል። ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም የሚገመገምበት ጥሩ የሠራና የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገበ የሚሸለምበትና ለበለጠ ሥልጣን የሚታጭበት፤ ሰነፉ ደግሞ የሚወቀስበትና ስልጣኑ የሚነጠቅበት ታላቅ በዓልም ነው ብለዋል። ይህም በብሄሩ ዘንድ ለዘመናት የተሻገረ የጠንካራ የሥራ ባህል ግንባታ መሰረት ሆኖ የቆየ መሆኑን አንስተዋል። ይህ ሁሉ ሲከናወን በማህበረሰባዊ የህግ ተገዥነት መሰረት መሆኑ የተለየ እንደሚያደርገው ገልጸው ከሁሉ በፊት ሰላምን በማስቀደም መንግስትንና ህግን ማክበር እንዲሁም ህግ የሚመራው ህዝብ የበላይ መሆኑን አመላካች ሥርዓት መሆኑን አንስተዋል። በዓሉ ከአዝመራ ጋር የተያያዘ የዘመን አቆጣጠርን ተከትሎ እንደሚከበርም የታሪክ ባለሙያው አቶ አሰፋ ይገልጻሉ። እንደ ታሪክ ተመራማሪው ገለጻ የካፋ ህዝብ አብዛኛው አርሶ አደር አልፎም አርብቶ አደር ሲሆን ለአዝመራ የተለየ ትኩረት ይሰጣል፤ በዓሉ ሊከበር 77 ቀናት ሲቀሩት ህዝቡ የአዲስ ዘመን መለወጫ ብሎ ሃምሌ አንድ አዝመራውን እንደሚጀምርም ጠቁመዋል። የአዝመራ ወቅት ሊገባደድ 25 ቀናት ሲቀሩት (ከሼ ዋጦ) ብሎ አዝመራውን ያጠናቅቃል። ወቅቱም ጨለማው አልፎ በብርሃን የሚተካበት፤ ክረምቱ ለበጋ ቦታውን የሚለቅበት በመሆኑ አዲስ አመት መድረሱን ያሳውቃል። ያን ጊዜ በጥንት የካፋ ምክርቤት ከሚገኙ ሰባት የሚክረቾ አባላት ውስጥ አንዱ የሆነው አዲዬ ራሾ ፤ የንጉሱ መቀመጫ በሆነው ቦንጌ ሸምበቶ በዓሉን ለማክበር ከየአቅጣጫው ለሚመጣው ህዝብ መንገዶችን በማፅዳት እና ለወንዞች ድልድይ በማበጀት በዓሉ መድረሱን ያበስራል። ያን ጊዜ በዓሉን ለማክበር ህዝብ ከያለበት አቅጣጫ ወደ ቦንጌ ሸምበቶ ይተማል። ህዝቡ በቦንጌ ሸምበቶ ከተሰበሰበ በኋላም ንጉሱ በተገኙበት የእያንዳንዱ ወራፌ ራሾ ሥራ ይገመገማል፤ ጥሩ ሥራ የሠራ ጠንካራ መሪ ይሸለማል፤ ለበለጠ ስልጣንም ይታጫል፤ ሀላፊነቱን በተገቢ ሁኔታ ያልተወጣው ደግሞ ይመከራል፣ ይወቀሳል አልፎም ስልጣኑን ይነጠቃል። ዛሬም ሀገራችን ይህ አይነቱን ጠንካራ የሥራ ባህል አብዝታ ትሻለች፤ እንዲህ አይነት ሀገር በቀል ዕውቀቶች ትውልዱን በጠንካራ ሥነ-ምግባርና የሥራ ባህል ለመገንባት ትልቅ ድርሻ አላቸው። በተጨማሪም በዓሉ ቅሬታዎችን ለመፍታትና ሰላምን ለማጠናከር ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ፤ ቂምና ጥላቻን ይዞ ወደ ንጉሱ ፊት መቆምም ይሁን ወደ አዲሱ ዓመት መሻገር ነውር ተደርጎ የሚወሰድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወደ በዓሉ ከመምጣቱ አስቀድሞም ይሁን በበዓሉ ወቅት የተጣላ ይታረቃል፤ ጥላቻም በፍቅር ይተካል ብለዋል የታሪክ ተመራማሪው። እንዲህ አይነቱ ሀገር በቀል ዕውቀት ጠንካራ ባህል ለመገንባት፤ ቅራኔዎችን በሰላም ለመፍታትና ማህበራዊ ግኑኝነቶችን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ ስላላቸው በትምህርት ሥርዓት ውስጥ አካቶ ማስተማርና ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ሲሉም ሃሳባቸውን አካፍለዋል። ሌላኛው የሀገር ሽማግሌና የካፋ፣ጫራ እና ናኦ የባህል ምክርቤት አባል አቶ ፀጋዬ ገብረማሪያም እንደሚሉት የካፋቾ ''የመኔ ሸድዬ ባሮ'' በዓል ማህበራዊ ግንኙነትን በማጠናከሩ ረገድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው በዓል ነው። ምክንያቱ ደግሞ፣ በዓሉን ለማክበር በአካባቢው ያሉ፣ በሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ እንዲሁም ባህር ማዶ የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆች የሚሰበሰቡበት ታላቅ በዓል ስለሆነ ነው ብለዋል። በዚህም የተራረቀ የሚገናኝበት፤ የተጠፋፋ የሚጠያየቅበት ሲሆን ህዝቡ በአንድ ላይ ተሰብስቦ በንጉሱ ተመርቆ፣ በልቶ ጠጥቶ እንዲሁም ተጫውቶ ወደ ቀጣዩ አመት በደስታና በታላቅ ተስፋ የሚሸጋገርበት እንደሆነም አብራርተዋል። ይህ ባህል በተለያዩ ምክንያቶች ከ120 ዓመታት በላይ ሳይከበር እንደቆየ የገለፁት አቶ ፀጋዬ ገብረማሪያም ዳግም መከበር ከጀመረበት ስምንት ዓመታት ወዲህ የነበረውን ታሪክና ባህል በሚያስቀጥል መልኩ በየዓመት በድምቀት እየተከበረ መሆኑንም አንስተዋል። ወጣቱ ትውልድ ባህሉንና ታሪኩን አውቆ እንዲኖርና እንዲያስቀጥል ግንዛቤ የመፍጠርና የማስተማር ሥራ በሰፊው እየተሠራ እንደሆነም ገልፀዋል። ከዚህ ባለፈም ባህሉንና ታሪኩን ለማስቀጠል የባህል ምክር ቤቱ የወረዳ የባህል ምክር ቤቶችን የማጠናከር፣ ታሪካዊ ቅርሶችን የመሰብሰብና የማደራጀት ሥራ እየሠራ ነውም ብለዋል። በዓሉ አንድነትን የሚያጠናክር፣ ጠንካራ የሥራ ባህልን የሚያበረታታ እና የተፈጥሮ ጥበቃን የሚያጠናክር በመሆኑ ከካፋ ብሔረሰብ በዓልነቱ ባለፈ የሀገርና የአለም ቅርስና ሀብት እንዲሆን ሰፊ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባም አቶ ፀጋዬ አሳስበዋል። የካፋቾ ዘመን መለወጫ በዓል (የመኔ ሸድዬ ባሮ) መሠረቱን ሳይለቅ ለትውልድ እንዲተላለፍ በዞን ደረጃ እየተሠራ መሆኑን የገለፁት የካፋ ዞን ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሃላፊ አቶ ተሾመ አምቦ ዘንድሮም ለዘጠነኛ ጊዜ በአደባባይ ለማክበር ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል። በዓሉ በሁሉም የካፋ ህዝብ በጋራ ያለምንም ልዩነት የሚከበር ታሪካዊ በዓል ሲሆን አለም አቀፋዊ እውቅና አግኝቶ በዩኔስኮ እንዲመዘገብ ለማስቻል ከተለያዩ ምሁራንና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመሆን የተለያዩ ጥናቶች እየተሠሩ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በበዓሉ ንጉሱ የተራቡትን የሚመግቡበት (ጮንጎ) የተሰኘ ስርዓት የሚፈፀምበትና የተጣሉ የሚታረቁበት ስርዓት እንደሚፈፀም የገለፁት አቶ ተሾመ አሁንም በዓሉ በየዓመቱ ሲከበር ይህ ሥርዓት ይከወናል ብለዋል። ቀጣይ ይህን በዓል በሰፊው አስተዋውቆ ወደ ቱሪዝም በማሳደግ ህዝቡ ከዘርፉ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችሉ ሥራዎች እንደተጀመሩም ሃላፊው ገልፀዋል። የዘንድሮው የ2016 ዓ.ም የካፊቾ ዘመን መለወጫ በዓል በቦንጋ ከተማ ከመስከረም 12 እስከ መስከረም 13/2016 ዓ.ም በፓናል ውይይትና በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበርም ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 5590
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 10559
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት። እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 4008
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል። “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 4859
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
መጣጥፍ
“ዮ-ማስቃላ''- ሁሉም የሚደሰትበት በዓል
Sep 23, 2023 821
በሳሙኤል አየነው የሰላም፣ የአብሮነት፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የአንድነት ተምሳሌት የሆነው የጋሞ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል “ዮ-ማስቃላ” ከወርሃ መስከረም አጋማሽ ጀምሮ በተለያዩ ባህላዊ ሁነቶች በድምቀት ይከበራል ። በተለያየ ምክንያት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ተራርቀው የነበሩ ወገኖች ወደ የአካባቢያቸው በመመለስ ከቤተሰቦቻቸው ብሎም ከቀየው ህብረተሰብ ጋር አብረው የሚያከብሩት የዓመቱ ታላቅ በዓል ነው ። ታዲያ በዓሉን በድምቀት ለማክበር ወንዶች ሰንጋ በሬ ለመግዛት እንዲሁም ለትዳር አጋሮቻቸውና ለልጆቻቸው ልብስና ጌጣ ጌጥ የሚሆን ገንዘብ መቆጠብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ሴቶችም ለባህላዊ ምግቦች፣ ለቅመማ ቅመም፣ ለቅቤና ለባህላዊ መጠጦች እህል ግዥ የሚሆን ገንዘብ ዓመቱን ሙሉ ሲቆጥቡ ይከርማሉ። መስከረም ወር ከገባበት ዕለት አንስተው ወንዶችም ሆኑ ሴቶቹ በቆጠቡት ገንዘብ በየፊናቸው ለበዓሉ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን ማቅረብ ይጀምራሉ። ይህም የዝግጅት ጊዜ “እንግጫ” በመባል ይጥራል። በ”ዮ--ማስቃላ” ጊዜ አብሮነት እንጂ ግለኝነት የሚባል ነገር በጋሞዎች ዘንድ ፈጽሞ አይታሰብም፤ አብሮ እርድ ማካሄድ፣ አብሮ መመገብ፣ አብሮ መጠጣት፣ አብሮ መጫወት የጋሞዎች መገለጫ ነው። እንደ ሌሎቹ በዓላት ሁሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችም በዓሉን እንዴት እናሳልፍ የሚል ስጋት አያድርባቸውም። ምክንያቱም የሌለውም ካለው ጋር አብሮ የሚቋደስበት፣ የሚደሰትበት፣ የሚተሳሰብበትና የሰብአዊነት ልክ የሚንጸባረቅበት ልዩ ድባብ ያለው በዓል ነውና ዮ-ማስቃላ ። የጋሞ የሀገር ሽማግሌ አቶ አመሌ አልቶ ስለ “ዮ--ማስቃላ” በዓል በትንሹ እንዲያወጉን ጠይቀናቸው በዓሉ ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን እንስሳትና አዕዋፋት ሁሉ የሚደሰቱበት እንደሆነ ነግረውናል። በአካባቢው ቋንቋ ተፈጥሮ ሁሉ በዓሉን በደስታ እንደሚያሳልፍ ለመግለጽ “ካፎስ ካናስ ማስቃላ” በማለት የሚገለጽ ስሆን “ለሰው ብቻ ሳይሆን ለእንስሳትም መስቀል ነው” እንደማለት ነው ብለዋል። በዓሉ ከመድረሱ ከሶስት ወራት አስቀድሞ በየአካባቢው ለእንስሳት የግጦሽ ሥፍራ ተከልሎ የሚዘጋጅ ሲሆን ችቦው በሚለኮስበት በደመራው ዕለት የቤት እንስሳት በሙሉ በዚያው የሚሰማሩ ይሆናል። ዓመቱን ሙሉ ሲያርሱ የነበሩ የእርሻ መሣሪያዎችም በበዓሉ ጊዜ ታጥበውና በቅቤ ታሽተው በክብር ይቀመጣሉ። ክብር ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለእንስሳትና ለእርሻ መሣሪያዎችም ይሰጣል። በባህሉ መሠረት ችቦ በሚወጣበት ሰዓት አባት የራሱን ችቦ ለኩሶ የቤቱን ምሰሶ፣ የከብቶችን ጋጣና የበር ጉበኖችን ግራና ቀኝ በችቦው ጫፍ በማነካካት ወደ ውጭ ካወጣ በኋላ ወንድ ልጆች የየራሳቸውን ችቦ ተራ በተራ እየለኮሱ አባታቸውን ተከትለው “ዮ---ማስቃላ” እያሉ ወደ ደመራ ቦታ ያመራሉ። ከዚያም አባት በቅድሚያ ችቦውን ከለኮሰ በኋላ ልጆች ደግሞ ተከትለው ደመራውን ይለኩሳሉ። ከዚህ ፕሮግራም መልስ ወደ ቤት ተመልሰው የተዘጋጀውን ገንፎ በአንድ ወጭት ላይ “ዮ--ማስቃላ”እያሉ ሁሉም የቤተሰብ አባላት፣ ዘመድ አዝማድና ጎረቤት ተሰባስበው በጋራ ይመገባሉ። በ”ዮ--ማስቃላ” በዓል በዋናነት እርድ የሚከወን ሲሆን ቁርጥ፣ ጎረድ ጎረድ፣ ክትፎና የወጣ ወጥ ዓይነቶች ተሠርተው ለምግብነት ይቀርባሉ። ከባህላዊ ምግቦች ደግሞ የገብስ ቅንጬ፣ የቆጮና ገብስ ውህድ ቂጣ፣ የቡላ ፍርፍር፣ ሀረግ ቦዬ፣ እንዲሁም ከመጠጥ አይነቶች ደግሞ ቦርዴ፣ ጠላ፣ የማርና የቦርዴ ጠላ ውህድና ሌሎች ተወዳጅ ምግቦችና መጠጦች ይዘጋጃሉ። በ”ዮ--ማስቃላ” በዓል ዕለት የሚቀራረቡ ጎረቤታሞች በጋራ ሆነው አማካይ በሆነ ሥፍራ ላይ የእርድ ሥነሥርዓት ያከናውናሉ። የእርድ ሥነ-ሥርአቱም በደመራው ዕለትና ማግስት እንደ ህብረተሰቡ ይሁንታ የሚፈጸም ይሆናል። ከማግስቱ ጀምሮ የተዘጋጀውን ሥጋ በጋራ እየበሉና እየጠጡ የበዓሉን ድባብ የሚያስቀጥሉ ሲሆን “ዱንግዛ” በተሰኘው የጋሞ ባህላዊ ጥበብ ልብስ ደምቀው በጌጣጌጥ አሸብርቀው ሁሉም በየአደባባዩ በባህላዊ ጫዋታዎች እየተደሰተ በዓሉን ያከብራል። ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነትና አብሮነት ካለ በአዲሱ ዓመት ምድሪቱ ተገቢውን ምርት እንደምትሰጥ ሁሉም ሰው በተሰማራበት መስክ ውጤታማ እንደሚሆን ይታመናል። ከዚም የተነሳ በአሮጌው ዓመት ሃዘን ላይ የነበሩ ወገኖች ሙሉ በሙሉ ሀዘናቸውን በመተው በአዲስ መንፈስ ወደ መደበኛው ህይወት ይመለሳሉ። የተጣሉ ወገኖች ቂም ይዘው አዲስ ዓመትን መሻገር በጋሞዎች ዘንድ ነውር በመሆኑ በባህላዊ ሸንጎ ሥርአት /ዱቡሻ/ በጋሞ አባቶች አሸማጋይነት እርስ በርስ ተነጋግረው በመታረቅ አዲሱን ዓመት በጋራ ያበስሩታል። በሌላ መንገድ “ዮ..ማስቃላ” በዓል ተጠብቆ ወጣቶች የሚተጫጩበት፣ የተጫጩት ደግሞ ጋብቻ የሚከውኑበት እንዲሁም ያገቡት በየገበያው ዕለት “ሶፌ” የሚባል ሥነ-ሥርዓት በማከናወን በማህበራዊ ህይወት ማህበረሰቡን በይፋ የሚቀላቀሉበት መሆኑን ጋሽ አመሌ አውግተውናል። ጋሞዎች ከሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች ጋር በመሆን በአብሮነት ለሁለት ሳምንታት በደስታ ካሳለፉ በኋላ ወደ ግብርና ሥራቸው በመመለስ ቀደም ሲል በክብር ያስቀመጧቸውን የእርሻ መሣሪያዎች በማንሳት ወደ እርሻ ሥራ ይገባሉ። እስከ ታህሳስ ወር መውጫ ድረስ የበዓሉ ድባብ ሳይጠፋ ይቆይና በመጨረሻም የመሰናበቻ ድግስ ወይም “ጮዬ ማስቃላ” በማዘጋጀት በህብረት ከተመገቡና ከጠጡ በኋላ የዓመት ሰው ይበለን፣ ዓመቱ የሰላም፣ የጤና፣ የበረከት ይሁን በማለት በመመራረቅ “ዮ--ማስቃላ”ን ይሸኛሉ። በዓሉ የህዝቡን ሰላም ፣አንድነትና አብሮነት የሚያንጸባርቅ ልዩ በዓል ነው በማለት የጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ አቶ ሞናዬ ሞሶሌ የጋሞ የሀገር ሽማግሌ የሆኑት የአቶ አመሌ አልቶን ሃሳብ ይጋራሉ። ባህላዊ እሴቱ ከትውልድ ወደ ትውልድ ተጠብቆ እንዲቆይ “ዮ--ማስቃላ” ትልቅ ድርሻ አለው። የባህል እሴቶች ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፉ በጥናትና ምርምር በማስገፍና የቋንቋና ባህል አውደ ጥናት በየዓመቱ እየተደረገ እንደሆነም ነግረውናል። አባቶች በልዩነት ውስጥ ያለንን አንድነት እንዳቆዩልን ሁሉ ወጣቶችም ኢትዮጵያዊ ለዛ ያላቸው የጋራ እሴቶች ሳይበረዙና ሳይከለሱ ጠብቀው ለትውልድ የማስተላለፍ ሃላፊነት አለባቸው የሚለውን የንግግራቸው ማሳረጊያ አድርገዋል።
የዕልፍ ሕጻናትን ዕጣ ፈንታ ከሞት ወደ ሕይወት የለወጠው ወጣት ላሌ ላቡኮ
Sep 8, 2023 1225
በሀገራችን በርካታ አካባቢዎች የታዳጊዎችን ተስፋና ህልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የሚገዳደሩ ከባህላዊ እምነት ጋር የተቆራኙ አይነተ ብዙ ጎጂ ባህላዊና ልማዳዊ ድርጊቶች እና ክዋኔዎች አሉ። ለአብነትም ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የተለመደው እና ከህጻናት ጥርስ አበቃቅል ጋር የተያያዘው ’ሚንጊ' የሚሰኘው ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ይጠቀሳል። በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣቸዋል። ከዚህ ጋር በማገናኘትም የሚወለዱ ህጻናት የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ከሆነ እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥመዋል። ይህ ልማድ “ሚንጊ” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን አያሌ ህጻናትን ቀጥፏል። ይህ ብቻም ሳይሆን የማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። ሚንጊ ተብለው የተፈረጁ ህጻናት በማህበረሰቡ ዘንድ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… እንደሚያመጡ ስለሚቆጠር ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል ዕጣ ይገጥማቸዋል። ሚንጊንና መሰል በየማህበረሰቡ ዘንድ ለዘመናት የተለመዱ ጎጂ ድርጊቶችን ለማስቀረት እና ማህበረሰብ አቀፍ ለውጥ ለማምጣት ግን ውስብስብ እና ጊዜ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው። ላሌ ላቡኮና መሰል ብርቱና አርቆ አሳቢ ሰዎች ግን ባደጉበት ብርቱ ጥረት የማህብረሰብን አስተሳስብ በመለወጥ ለዘመናት ለሚከወኑ ውስብስብ ችግሮችን መፍትኤ መስጠት ችለዋል። ላሌ ላቡኮ በተወለደበት ቀዬ እና አባል በሆነበት ደመ ከልብ ሆነው የሚቀሩ ህጻናትን ዕጣ ፈንታ ከወንዝ፣ ከገደልና ከጫካ ከመጣል ተርፈው ለወግና ማዕረግ እንዲበቁ አስችላል። በአጉል ባህል ሕይወታቸውን የሚነጠቁ ዕልፍ አዕላፍ ህጻናት ነፍስ እንዲዘሩ በማድረግ ትውልድ ያሻገረ፣ ማህበረሰብን የለወጠ አርበኛ ነው። ላሌ ላቡኮ ይህን ነባር ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ለመቃወምና መፍትሄ ለማምጣት ያነሳሳው ሁለት እህቶቹን ጨምሮ ምንም ነፍስ ያላወቁ ሕጻናት በሚንጊነት ተፈርጀው ሲቀጠፉ በማየቱና በመስማቱ እንደሆነ ይናገራል። ከ17 ዓመታት በፊት ‘ኦሞ ቻይልድ’ በሚል ባቋቋመው ድርጅት 'ሚንጊ' የተባሉ 58 ሕፃናትን ከገዳዮች ፈልቅቆ ከሕልፈት ወደ ሕይወት ለውጧል፣ ለቁም ነገር ለማብቃትም እያስተማራቸው ይገኛል። እህቶቹን ጨምሮ የትውልድ መንደሩ ሕጻናትን ሕይወት ለመቀጠፍ የዳረጋቸው የሚንጊ ድርጊት የሚፈጸመው፣ በማህበረሰቡ ዕውቀት ማነስ ነው ብሎ ያምናል። በዚህም ይህን አስከፊ ድርጊት እና አስተሳሰብ ለመቀየር ቆርጦ በመነሳቱ ቤተሰቡን ጨምሮ ከማህበረሰቡ መገለል እስከ ማስፈራሪያ ጥቃቶች አስተናግዷል። እርሱ ግን ፈተናዎች ሳይበግሩት በዓላማው ጸንቶ፣ ትዕግስትና ብልሃት ተላብሶ ሸውራራ ማህበረሰብ አቀፍ አመለካከቶችን መስበር ችሏል። የሚንጊ ባህል አሁንም ሙሉ ለሙሉ እንዳልተቀረፈ የሚናገረው ላሌ፣ ስር ነቀል የአስተሳስብ ለውጥ ለማምጣት ለህብረተሰቡ አሁንም ብርቱ ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎች እንደሚገቡ ገልጿል። ላሌ በመሰረተው ድርጅት ከሚማሩ ሕጻናት ባሻገር ከ300 በላይ ህጻናት ከቤተሰባቸው ዘንድ ሆነው ለመማር እንዲችለኩ ማድረጉንም ይናገራል። ሕፃናቱን ከሞት አፋፍ ታድጎ ከራሳቸው ሕልውና ባለፈ ለቁም ነገር እንዲበቁና ለሀገርና ለወገን የሚበጁ ሰዎች እንዲሆኑ በመስራቱ አዕምራዊ እርካታ እንደሚሰማው ይገልጻል። ላሌ የሚንጊን ጎጂ ድርጊት ከመታደጉ በተጨማሪ በደቡብ ኦሞ ትምህርት ቤት ገንብቶ ከ700 በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል። ናሽናል ጂኦግራፊ፣ ቴድ ቶክ፣ የሰብዓዊ መብቶች ተቋም እና የበጎ ሰው ሽልማት ድርጅት የላሌን ትውልድ የመታደግ ተግባር ዕውቅና ከሰጡት ወስጥ ይጠቀሳሉ።