ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚደረገው ዘርፈ ብዙ ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Mar 4, 2026 12
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እያደረገ ያለውን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ገለፁ። በኢትዮጵያ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ሂደት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ነው የብሄራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ካውንስል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በሸገር፣ በቢሾፍቱ እና በአዳማ ከተሞች በሚገኙ ልዩ ልዩ አምራች ኢንዱስትሪዎች በመገኘት የመስክ ምልከታ አድርገዋል። የመስክ ምልከታው በኢንዱስትሪዎች አካባቢ ያሉ ማነቆዎችን በቅርበት ለመረዳትና በካውንስሉ አማካኝነት ፈጣን መፍትሄ ለመስጠት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል። የካውንስሉ አባል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባንኩ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እያደረገ ያለውን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል። ባንኩ በዘርፉ ያሉ እውነተኛ ችግሮችን በመለየት በፋይናንስና በውጭ ምንዛሬ በኩል የሚጠበቅበትን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሚሰጠው አጠቃላይ ብድር ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የያዘው የኢንዱስትሪ ፋይናንስ እንደሆነ ነው ፕሬዝዳንቱ የተናገሩት። ከባንኩ የብድር ሴግሜንቶች መካከል ከ45 በመቶ በላይ የሚሆነው ለአምራች ኢንዱስትሪው የቀረበ መሆኑንም ገልጸዋል። አምራች ድርጅቶች አሁንም ተጨማሪ የፋይናንስ አቅርቦት እንደሚፈልጉ የገለጹት አቶ አቤ ሳኖ፣ ባንኩ ይህንን ፍላጎት ለመሙላት ትኩረት መስጠቱን ጠቁመዋል። አጠቃላይ የፋይናንስ አቅምን ማሳደግ ይፈልጋል፤ እኛም የተሻለ ትኩረት ማድረግ እንዳለብን ተረድተናል ሲሉም ፕሬዚዳንቱ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያን የሚገነባት እና የሚያጸናት የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ
Mar 4, 2026 27
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ ለሀገራዊ መግባባት በምክክሩ የሚያደርገውን አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል። ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት ተችሏል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 የተቋቋመው፣ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ መሠረታዊ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት እና በሕዝቦች መካከል የጋራ መግባባትን ለመፍጠር ነው። ኮሚሽኑ አካታች የሆኑ የምክክር መድረኮችን በማመቻቸት ለዘላቂ ሰላም እና ለጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚረዱ ምክረ ሀሳቦችን የማቅረብ ግብም አለው። ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥ በየክልሎቹና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተወካዮች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎችን በስፋት አከናውኗል። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ብልፅግና ፓርቲ ምክክር ኢትዮጵያን ጠንካራ ሀገር ያደርጋታል የሚል ፅኑ እምነት እንዳለው ገልፀዋል። ብልፅግና ፓርቲ በሀገራዊ ምክክር የእስካሁን ሂደት ውስጥ ግልፅ የሆነ አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መቆየቱንም አስታውሰዋል። የምክክር ሂደት ለዘመናት የተሻገረና ከሀገረ መንግስት ግንባታ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በዘመናት መካከል በተለያዩ ምክንያቶች የተፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው ያሉት አቶ መለሰ፤ ፓርቲው ምክክርን የአንድ ወገን ሥራ አድርጎ እንደማይመለከተውም ተናግረዋል። ምክክሩ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ መሆኑን በማመን፣ ፓርቲው በውይይት በመሳተፍና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ይበጃሉ ያላቸውን አጀንዳዎች በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። እንደ ገዥ ፓርቲም ሂደቱ እንዲሳካ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን አክለዋል። የምክክር ሂደቱ ለስምንት ወራት መራዘሙ ኮሚሽኑ ሥራውን በአግባቡና በጥራት እንዲያጠናቅቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ብልፅግና ፓርቲም በቀጣይ ወራት ለሀገራዊ መግባባት እየተካሄደ ላለው ምክክር አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በዚህም ፓርቲው ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ የመግባባት ደረጃ ላይ እንድትደርስ ይሰራል ብለዋል። ብልፅግና ፓርቲ የምክክር ሂደት ለትውልድ የሚኖረውን የላቀ ፋይዳ በሚገባ የሚገነዘብ በመሆኑ አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሁሌም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በስፔን ጥሎ ማለፍ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ሪያል ሶሲዬዳድ ከአትሌቲኮ ቢልባኦ የመልስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ
Mar 4, 2026 66
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ሪያል ሶሲዬዳድ ከአትሌቲኮ ቢልባኦ በስፔን ጥሎ ማለፍ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታቸውን ዛሬ ያከናውናሉ። በፕሪሚየር ሊጉ አርሰናል ከብራይተን ማንችስተር ሲቲ ከኖቲንግሃም ፎረስት የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ ጨዋታው ምሽት አምስት ሰዓት ላይ በአኖኤታ ስታዲየም ይካሄዳል። ሁለቱ ቡድኖች የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ በቤናት ቱሪንቴስ ግብ ሪያል ሶሲዬዳድ 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ሪያል ሶሲዬዳድ ከሜዳው ውጪ ባስመዘገበው ድል በአንጻራዊነት ለፍጻሜ የማለፍ እድል በእጁ ይዟል። የባስኩ ክለብ ሪያል ሶሲዬዳድ ሁለት ጊዜ የስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫን አንስቷል። ለመጨረሻ ጊዜ ውድድሩን ያሸነፈው እ.አ.አ በ2019/20 የውድድር ዓመት ነው። ሌላኛው የባስክ ክለብ አትሌቲኮ ቢልባኦ 24 ጊዜ የስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫን በማሸነፍ ከባርሴሎና በመቀጠል ስኬታማው ክለብ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ። ቢልባኦ ለመጨረሻ ጊዜ ውድድሩን ያሸነፈው እ.አ.አ በ2023/24 የውድድር ዓመት ነበር። በደርሶ መልስ የሚያሸንፈው ቡድን በፍጻሜው ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ይገናኛል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ መርሐ-ግብር አትሌቲኮ ማድሪድ ባርሴሎናን በድምር ውጤት 4 ለ 3 በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፏል።
በፕሪሚየር ሊጉ አርሰናል ከብራይተን ማንችስተር ሲቲ ከኖቲንግሃም ፎረስት የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Mar 4, 2026 78
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ29ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ አምስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ብራይተን ከአርሰናል በአሜክስ ስታዲየም ይጫወታሉ። ብራይተን በ37 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። አርሰናል በ64 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ጨዋታው ብራይተን ሶስተኛ ተከታታይ የሊግ ድሉን ለማስመዝገብ የሚያደርገው ነው። ተጋጣሚው አርሰናል ካሸነፈ የሊጉን መሪነት የሚያጠናክርበት ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያገኛል። የ40 ዓመቱ ክሪስ ካቫናግ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ማንችስተር ሲቲ ኖቲንግሃም ፎረስትን ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ላይ በኢትሃድ ስታዲየም ያስተናግዳል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ማንችስተር ሲቲ በ59 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ኖቲንግሃም ፎረስት በ27 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል። ማንችስተር ሲቲ ማሸነፍ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ እንዲቀጥል ያደርገዋል። ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች ያላሸነፈው ኖቲንግሃም ፎረስት ማሸነፍ ላለመውረድ በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያስገኝለታል። የ40 ዓመቱ ዳረን ኢንግላንድ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። ምሽት 5 ሰዓት ከ15 ላይ ኒውካስትል ዩናይትድ ከማንችስተር ዩናይትድ ይጫወታል። ኒውካስትል ዩናይትድ በ36 ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ማንችስተር ዩናይትድ በ51 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ኒውካስትል ከሁለት ተከታታይ ሽንፈቶች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። በማይክል ካሪክ ስር ድንቅ ግስጋሴ እያደረገ የሚገኘው ማንችስተር ዩናይትድ በመልካም ጉዞው ለመቀጠል እና የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ፉክክሩን ለማጠናከር ሶስት ነጥብ ማግኘት ወሳኝ ነው። በቪላ ፓርክ ስታዲየም አስቶንቪላ ከቼልሲ ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ላይ ይጫወታሉ። አስቶንቪላ በ51 ነጥብ አራተኛ፣ ቼልሲ በ45 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዘዋል። በሻምፒዮንስ ሊግ ለመሳተፍ የሚፎካካሩት ሁለቱ ቡድኖች ጠንካራ ፍልሚያ ያደጋሉ። ፉልሃም ከዌስትሃም ዩናይትድ ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ላይ በክራቨን ኮቴጅ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከፋሲል ከነማ ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Mar 4, 2026 59
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 22ኛ ሳምንት ዛሬም ቀጥሎ ሲውል አራት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ሲዳማ ቡና ከፋሲል ከነማ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ የተመልካቾችን ትኩረት ስቧል። ሲዳማ ቡና በሊጉ ካደረጋቸው 21 ጨዋታዎች መካከል 10ሩን ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በዘጠኝ ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በ21ዱ ጨዋታዎች ላይ 26 ጎሎችን ሲያስቆጥር 11 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ39 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው ፋሲል ከነማ በሊጉ 21 ጨዋታዎችን አድርጎ በስምንቱ አሸንፎ በአራቱ ተሸንፎ በቀሪ ስምንት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 16 ግቦችን ሲያስቆጥር 13 ጎሎችን አስተናግዷል። ፋሲል ከነማ በ33 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ሲዳማ ቡና ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ እና የሊጉን መሪነት ለማጠናከር ይጫወታል። ፋሲል ከነማ ካሸነፈ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል ይመለሳል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ወላይታ ድቻ ከሃዋሳ ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ወላይታ ድቻ እስከ አሁን በሊጉ 21 ጨዋታዎችን አድርጎ አራት ጊዜ ሲያሸንፍ ሰባት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ 10 ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 22 ግቦችን ሲያስቆጥር 24 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ22 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ በበኩሉ በሊጉ ባከናወናቸው 21 ጨዋታዎች በ10ሩ ሲያሸንፍ በአምስቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በስድስር ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 24 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 13 ግቦች ተቆጥረውበታል። የሁለት ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ሃዋሳ ከተማ በ36 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ወላይታ ድቻ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ እና ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት ይጫወታል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ ድል ከቀናው ከሁለት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ይመለሳል። ሁለቱ ጨዋታዎች በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከባህር ዳር ከተማ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ኢትዮጵያ ቡና በ26 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ባህርዳር ከተማ በ27 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ኢትዮጵያ ቡና ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ ባህርዳር ከተማ በ21ኛ ሳምንት በአርባምንጭ ከተማ ካስተናገደው ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። አርባምንጭ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። በሊጉ ሁለት ድሎችን ብቻ ያስመዘገበው አርባምንጭ ከተማ በ16 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ28 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ጨዋታው አርባምንጭ ከተማ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያን የሚገነባት እና የሚያጸናት የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ
Mar 4, 2026 27
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ ለሀገራዊ መግባባት በምክክሩ የሚያደርገውን አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል። ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት ተችሏል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 የተቋቋመው፣ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ መሠረታዊ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት እና በሕዝቦች መካከል የጋራ መግባባትን ለመፍጠር ነው። ኮሚሽኑ አካታች የሆኑ የምክክር መድረኮችን በማመቻቸት ለዘላቂ ሰላም እና ለጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚረዱ ምክረ ሀሳቦችን የማቅረብ ግብም አለው። ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥ በየክልሎቹና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተወካዮች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎችን በስፋት አከናውኗል። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ብልፅግና ፓርቲ ምክክር ኢትዮጵያን ጠንካራ ሀገር ያደርጋታል የሚል ፅኑ እምነት እንዳለው ገልፀዋል። ብልፅግና ፓርቲ በሀገራዊ ምክክር የእስካሁን ሂደት ውስጥ ግልፅ የሆነ አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መቆየቱንም አስታውሰዋል። የምክክር ሂደት ለዘመናት የተሻገረና ከሀገረ መንግስት ግንባታ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በዘመናት መካከል በተለያዩ ምክንያቶች የተፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው ያሉት አቶ መለሰ፤ ፓርቲው ምክክርን የአንድ ወገን ሥራ አድርጎ እንደማይመለከተውም ተናግረዋል። ምክክሩ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ መሆኑን በማመን፣ ፓርቲው በውይይት በመሳተፍና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ይበጃሉ ያላቸውን አጀንዳዎች በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። እንደ ገዥ ፓርቲም ሂደቱ እንዲሳካ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን አክለዋል። የምክክር ሂደቱ ለስምንት ወራት መራዘሙ ኮሚሽኑ ሥራውን በአግባቡና በጥራት እንዲያጠናቅቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ብልፅግና ፓርቲም በቀጣይ ወራት ለሀገራዊ መግባባት እየተካሄደ ላለው ምክክር አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በዚህም ፓርቲው ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ የመግባባት ደረጃ ላይ እንድትደርስ ይሰራል ብለዋል። ብልፅግና ፓርቲ የምክክር ሂደት ለትውልድ የሚኖረውን የላቀ ፋይዳ በሚገባ የሚገነዘብ በመሆኑ አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሁሌም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በትግሪኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ካስተላለፏቸው መልዕክቶች
Mar 3, 2026 98
ለትግራይ ሕዝብና ወጣቶች ያስተላለፉት መልዕክት፡- "የትግራይ ሕዝብ ከጦርነት ይልቅ ሰላምና ልማት ይገባዋል" ብለዋል። ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁ መክረዋል። መንግሥት በትግራይ ክልል ሰላም እንዲሰፍንና ዳግም ጦርነት እንዳይከሰት ጽኑ ፍላጎት እንዳለውና ለዚህም ማንኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል አረጋግጠዋል። የሰሜኑን ጦርነት መንስኤዎች በተመለከተ ህወሓት ከ50 ዓመት በፊት በነበረ ኋላቀር አስተሳሰብ የታሰረ መሆኑና ለውጥን ለመቀበል አለመፈለጉ። ዓለም በቴክኖሎጂና በ"ፕራግማቲዝም" በምትመራበት ዘመን፣ ድርጅቱ በአሮጌው መንገድ ለመጓዝ መሞከሩ ለግጭት ዳርጎታል። ቆሞ ቀሩ ኃይል "ኢትዮጵያ ትፈርሳለች" የሚል የተሳሳተ ስጋት በመዝራት የለውጡን ኃይል እንደ ጠላት ማየቱ። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተግባራዊነት በተመለከተ ፡- መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ሰላም እንዲያገኝ ባንክ፣ መብራትና ቴሌኮም የመሳሰሉ አገልግሎቶችን በፍጥነት እንዲመለሱ ማድረጉን ገልጸዋል። ሆኖም ቆሞ ቀሩ ቡድን ስምምነቱን "መርጦ የመተግበር" ዝንባሌ እያሳየ መሆኑን ተችተዋል። በተለይም ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ውሳኔ አለማክበሩን ጠቅሰዋል። ድርጅቱ ለልማት የተመደበውን በጀት ለጦርነት ዝግጅትና ለታጣቂዎች ቀለብ እየዋለ መሆኑን ገልጸው፣ ይህም በትግራይ ሕዝብ ላይ ተጨማሪ መከራ እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በጦርነቱ ወቅት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ፡- ጦርነት ሁልጊዜም አስከፊ ገጽታ እንዳለው ገልጸው፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የሽግግር ፍትሕ (Transitional Justice) አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ ሂደት ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ በሆነ መንገድ ሊካሄድ እንደሚገባውና ወንጀል የፈጸሙ አካላት በሕግ መጠየቅ እንዳለባቸው ገልጸዋል። የኤርትራ መንግሥት (ሻዕቢያ) ሚና በጦርነቱ ወቅት የኤርትራ ጦር ያደረገው ድጋፍ የሚታወስ መሆኑን ጠቅሰዋል። ሆኖም በጦርነቱ ሂደት የተፈጸሙ ማናቸውም ዓይነት ጥፋቶች፣ ግድያዎችና ዘረፋዎች (በተለይም በአክሱም፣ ዓድዋና ሽሬ አካባቢዎች) የማይቀበሉትና የሚወገዝ ተግባር መሆኑን በግልጽ አስታውቀዋል። መንግሥት ማንኛውንም የውጭ ኃይል ጣልቃ ገብነት እንደሚቃወምና የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር እንደሚሠራ ገልጸዋል።
የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤን የማስቀጠል አባዜ ምክንያት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Mar 3, 2026 73
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው የህወሓት አመራር ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤ የማስቀጠል አባዜ ምክንያት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ ቆይታ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የሰሜኑ ጦርነት መነሻ ምክንያቶችን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፤ ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና እኔ ብቻ በሚል ስሜት በመዋጡ ግጭት እንዲነሳ መንስኤ መሆኑን ገልጸዋል። ህወሓት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብ የታሠረ ድርጅት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ብቻ ሳይሆን ዓይኑን ጨፍኖ ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ ርምጃዎችን ሲወስድ መቆየቱንም ተናግረዋል። የለውጡ ኃይል የጀመረውን ጉዞ ለማደናቀፍ መሞከሩን ገልጸው፤ በህወሓት ቆሞ ቀር አስተሳሰብ የተነሳው ጦርነት ጉዳት ማስከተሉንም አንስተዋል። ሁለተኛው ቁልፍ ምክንያት ደግሞ ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ ጋር የተሣሠረ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ህወሓት ኢትዮጵያ በጥርጣሬና በሥጋት ውስጥ እንድትኖር መስራቱ ለችግሮች መባባስ ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል። ቆሞ ቀሩ ኃይል ከ50 ዓመት በፊት ከነበረው አስተሳሰብ ውጭ ሊንቀሳቀስ አለመቻሉን ጠቅሰው፤ ይህ ደግሞ ከለውጡ ጋር አብሮ ለመሄድ እንዳላስቻለው ገልጸዋል። የለውጥ ኃይሉ ዓለምን ያስደመመ ተአምራዊ ለውጦችን ማምጣቱን ጠቅሰው፤ ቆሞ ቀር ኃይሉ ከለውጥ ኃይሉ ጋር ተስማምቶ ሕዝቡንና ነፍሱን እንደመለወጥ የልማት ሽታ ከማያውቁ ኋላቀሮች ጋር እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ ያለው የፖለቲካ ስብራት ሌላኛው መንስኤ እንደሆነ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተሳሳተ ትርክት ላይ የተመሰረተው ፖለቲካዊ መዋቅር የፖለቲካ ስርዓቱ እንዲበላሽ ማድረጉን ነው ያብራሩት። ጦርነቱ የራሱ ልዩ ገጽታዎች እንዳሉት ሆኖ ከሀገራዊ መዋቅር ችግር የተለየ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባውም ብለዋል። ይህ አዙሪት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መሰበር አለበት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይሄንን ለመስበር ደግሞ ኃላፊነት መውሰድ እንደሚገባ ገልጸዋል። እንደ ትውልድ ይበቃል ብለን መሥራት አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የመንግስት አቋም ችግሮችን በውይይት መፍታት አማራጭ የሌለው መንገድ እንደሆነ በጽኑ እንደሚያምንም ገልጸዋል። ይሄንን ለማድረግ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ወሳኝ ሀገራዊ መፍትሔ ሊሆን ይችላል ብለን እናምናለን ብለዋል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ እስካሁን ከሞላ ጎደል ከትግራይ ውጭ አብዛኛው ሥራ እየተገባደደ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በትግራይ ክልል ግን ውይይት እንዳይደረግ፣ ሕዝባችን ቁጭ ብሎ እንዳይወያይ፣ ጥያቄ አንሥቶ መፍትሔ እንዳያገኝ፣ ያ ቆሞ ቀር ኃይል ሆን ብሎ እየሠራ ይገኛል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ደግሞ ትክክለኛ አካሄድ ነው ብዬ አላምንም ብለዋል።
ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት ተችሏል
Mar 3, 2026 96
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት መቻሉን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። ዛሬ "የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት እመርታ፤ ለተሳካ ሀገረ መንግሥት ግንባታ!" በሚል መሪ ሀሳብ በዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት ቅንጅት ላይ የሚያተኩር ሀገራዊ መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምሕረት የፍርድ ቤቶች የለውጥ ተግባራትን አስመልክቶ ባቀረቡት የመነሻ ሐሳብ፤ የዳኝነት ነጻነትን ለማጠናከር የሕግ ማሻሻያ መደረጉን ተናግረዋል። ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ አኳያም ግልጽ ችሎትን የማስፋፋት ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፤ ግልጽ ችሎት ከነበረበት 65 በመቶ ወደ 91 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። ፍርድ ቤቶች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ድምፅን ወደ ጽሁፍ የሚቀይር ቴክኖሎጂን በመጠቀም ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ኮሚሽኑ እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እስካሁን ውጤታማ የሚባሉ ሥራዎችን ሰርቷል ብለዋል። የሀገሪቱን ሁሉንም ክልሎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ 93 በመቶ ማካተት መቻሉን ጠቁመው፤ በቀጣይም አጀንዳ መቅረጽና ይፋ ማድረግ እንዲሁም ሀገራዊ ምክክር ማካሄድ ከሚከናወኑ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ የቦርዱን የለውጥ እና ቀጣይ ተግባራት ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ቦርዱ ባለፉት ዓመታት ተቋማዊ የሕግ ማሻሻያዎችን በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዕጩዎችን ምዝገባ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል በማከናወን ማጠናቀቅ መቻሉን ተናግረው፤ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ስልጠና መሰጠት መቻሉንም ገልጸዋል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬታማነት ለማከናወን "ምርጫዬ" የመራጮች መመዝገቢያ የዲጂታል አማራጭ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ባቀረቡት የመነሻ ጽሑፍ፤ ነጻና ገለልተኛ ተቋም ለመገንባት የአዋጅ ማሻሻያ፣ ደንብና መመሪያዎችን ማሻሻል መቻሉን ገልጸዋል። ከኦዲት ሽፋን አኳያም የፋይናንሻል ኦዲት መቶ በመቶ ማከናወን መቻሉን በመጥቀስ፤ የክዋኔ ኦዲትንም ከ24 ወደ 41 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል። የኢትየጵያ ሕዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕምባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ከለውጡ ወዲህ በተከናወኑ የለውጥ ስራዎችም ከአሰራርና ከሰው ሃይል አኳያ፣ የሕግ ማሻሻያ ተግባራት፣ ከቴክኖሎጂ አኳያ እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራሮች ተዘርግተው ስኬታማ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። ከቴክኖሎጂ ስራዎች ለግልጸኝነት፣ ለተጠያቂነት፣ ለቅልጥፍና እንዲሁም ለውጤታማነት ምቹ መደላድል መፍጠራቸውን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ባቀረቡት የመነሻ ጽሑፍ፤ ከለውጡ በፊት ኮሚሽኑ ገለልተኛ እና ውጤታማ ያልነበረ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ምቹ የሕግ ማዕቀፍ፣ አዲስ የሰው ሃብት መዋቅር፣ ብቃትና አቅም ያለው አመራር መፍጠር፣ ሥራን የሚያቀላጥፉ በቴክኖሎጂ የተደገፉ መፍትሔዎች፣ የመረጃ ስርዓት በቴክኖሎጂ የሚመራ መደረጉ እንዲሁም የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ መቻሉን ጠቁመዋል። የመድረኩ ታሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉን አድንቀዋል፡፡ ይህም ለሀገረ መንግስት ግንባታ ብሎም ለዘላቂ ልማትና ለሕዝቦች ተጠቃሚነት መረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በሰጡት ማጠቃለያ፤ ለምክር ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት በሕግ የተሰጣቸውን ሥልጣንና ኃላፊነት በገለልተኝነትና በነፃነት እየተወጡ ይገኛሉ። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዳኝነትና ዲሞክራሲ ተቋማት ላይ መሠረታዊ የሪፎርም ሥራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። ተቋማቱ ላይ ከተከናወኑ የለውጡ ስራዎች መካከል የማቋቋሚያ አዋጆቻቸውን በድጋሚ መፈተሽና ማሻሻል፣ የአመራር ሥርዓታቸውን ይበልጥ ውጤታማ ማድረግ፣ ዘመናዊና ግልጽነት ያለው የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት መቻል ዋና ዋናዎቹ ናቸው ብለዋል፡፡ የተቋማት ግንባታ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ ነው ያሉት አፈ-ጉባኤው፤ ተቋማቱ ነፃ ሆነው እንዲሠሩ መደረጉ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና ዴሞክራሲን እውን ለማድረግ ትልቅ መሠረት እንደሚጥል አጽንኦት ሰጥተዋል። ተቋማቱ በገለልተኝነት መሥራታቸው ጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን ለማፋጠን ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም ጠቁመዋል።
የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) ከአፍሪካ ሀገራት የመከላከያ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ
Mar 3, 2026 85
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) ከአፍሪካ ሀገራት የመከላከያ ሚኒስትሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ የተደረገው 130ኛው የዓድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች ኮንፈረንስ ጎን ለጎን ነው። የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ከመጡ የመከላከያ ሚኒስትሮችና የልዑካን ቡድን መሪዎች ጋር ውጤታማ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ማድረጋቸውን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ወቅት ቀደም ሲል በሀገራቱ መካከል የተፈረሙ የትብብር ስምምነቶች ያሉበት የአፈፃፀም ደረጃ በጥልቀት የተገመገመ ሲሆን፣ በቀጣይም ትብብሩን ይበልጥ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ አዳዲስ የመግባቢያ ሰነዶችን ጨምሮ በልዩ ልዩ የሥራ መስኮች ላይ በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ተደርሷል። ሚኒስትሯ በውይይቱ ወቅት እንደገለፁት፤ የዓድዋ ድል ከታሪካዊ ፋይዳው ባሻገር ዛሬ አፍሪካ ከፊቷ የተደቀኑባትን ወቅታዊ የፀጥታና የደኅንነት ስጋቶች በጋራ ለመመከት እንደ ትልቅ የመንፈስ ምንጭና የትብብር ማዕቀፍ ሊያገለግል ይገባል። በመሆኑም የአህጉሪቱን ሰላምና መረጋጋት ለማረጋገጥ የሚያስችል የጋራ ግንዛቤ በመያዝ፣ በአንድነትና በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። በተለይም በወታደራዊ ቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሥልጠናና በልምድ ልውውጥ መስኮች በጋራ ለመሥራት መግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን፣ ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ የፀጥታ ስጋቶችን በጋራ ለመከላከል የሚያስችሉ ስልታዊ የትብብር አቅጣጫዎችም ተቀምጠዋል። በውይይቱ የተሳተፉት የአፍሪካ ሀገራት የመከላከያ ሚኒስትሮች በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ለአህጉራዊ ሰላምና መረጋጋት እያበረከተች ያለውን ቀዳሚና የማይተካ ሚና አድንቀዋል። የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነውን የዓድዋ ድል በዓልን በኢትዮጵያ ተገኝተው ከወንድሞቻቸው ጋር በጋራ በማክበራቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ደስታ ገልፀው፣ በቀጣይም በጋራ የመከላከል አቅም ግንባታ ላይ በቁርጠኝነት ለመሥራት ያላቸውን ፅኑ ፍላጎት አረጋግጠዋል። የሁለትዮሽ ውይይቱ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነት ከማሳደጉም ባለፈ፣ የአህጉሪቱን የጋራ ደኅንነትና ትስስር ለማረጋገጥ የሚደረገውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል። ሚኒስትሯ ውይይት ካደረጉባቸው ሀገራትና ተቋማት መካከል የኬንያ፣ የደቡብ ሱዳን፣ የዚምባብዌ፣ የዛምቢያ፣ የኮንጎ ሪፐብሊክ ፣የቦትስዋና፣ የሩዋንዳ፣ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ የካሜሩን፣ የማሊ እና የአልጄሪያ የመከላከያ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ ጄኔራሎች እንዲሁም የምሥራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ይገኙበታል።
የወርሃ ጥር እና የካቲት 𝟐𝟎𝟏𝟖 የስራ ትግበራዎች ማጠቃለያ
Mar 3, 2026 126
በሁለቱ ወራት ፈር ቀዳጅ የዲጂታል አገልግሎቶች፣ መጠነ ሰፊ የመሠረተ ልማት እና የኢኮ-ቱሪዝም ልማቶች የተመረቁበት እንዲሁም ስትራቴጂካዊ ዓለም አቀፍ ትብብሮች የተጠናከሩበት ነበር። የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ𝟔ኛው የሥራ ዘመን 𝟏𝟎ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ የኢኮኖሚ እና ፖለቲካዊ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከአባላቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ኢትዮጵያ በዓመቱ መጨረሻ የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ጠቁመዋል። በሪፎርሙ ማግስት መንግሥት አንድም የንግድ ብድር ባለመውሰዱ የሀገሪቱን የዕዳ ጫና መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል። ባለፉት ስድስት ወራት ከሸቀጥ ኤክስፖርት 5.1 ቢሊዮን ዶላር (የዕቅዱን 120 በመቶ)፣ ከአገልግሎት ዘርፍ 4.5 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም ከሬሚታንስ 4.6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ይፋ አድርገዋል። በቴክኖሎጂ ረገድም የአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ኢንስቲትዩት መቋቋሙን እና በዓለም ሁለተኛ የሆነው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ሊከፈት መሆኑን፣ የሞባይል ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን እንዲሁም የሞባይል ገንዘብ ተጠቃሚዎች 58 ሚሊዮን መድረሳቸውን ገልጸዋል። ብሔራዊ ሰላምን በተመለከተ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት እንደሚገባ፣ የወልቃይት ነዋሪዎች በሰላም የመኖር መብት እንዳላቸው እና የትግራይ ሕዝብ በፖለቲካው መድረክ ዋና ተዋናይ መሆን እንዳለበት አሳስበዋል ። መሠረተ ልማት እና የከተማ ትራንስፎርሜሽን:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መጠነ ሰፊ የመሠረተ ልማት ክንውኖችን በመጎብኘት እና በማስጀመር የሀገሪቱን የዘመናዊነት ጉዞ በተግባር ያረጋገጡበት ወር ነበር። በሀዋሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ የተመለከቱ ሲሆን፣ በነቀምቴ ከተማም ዘመናዊ የትራፊክ አስተዳደር እና ከመሬት በታች የሚዘረጉ የመሠረተ ልማት ሥርዓቶችን ያካተተውን የኮሪደር ልማት ሥራ ጎብኝተዋል ። ግብርና፣ መስኖ እና የምግብ ሉዓላዊነት:- የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዋና ዋና የግብርና ስፍራዎች የመስክ ምልከታ አድርገዋል። በ"ሌማት ትሩፋት" መርሐ ግብር በሀዋ ገላን ወረዳ የለማውን የሙዝ ክላስተር የጎበኙ ሲሆን፣ ለተለያዩ ሰብሎች አስተማማኝ የውሃ አቅርቦት የሚሰጠውን የቄጦ መስኖ መሠረተ ልማት ፕሮጀክትንም ተመልክተዋል ። በተጨማሪም የአርጆ ዲዴሳ መስኖ ፕሮጀክት ያለበትን ደረጃ የገመገሙ ሲሆን፣ በብላቴ ወንዝ አካባቢ በግል ባለሀብቶች እየለሙ ያሉ የፍራፍሬ ልማቶችን ጎብኝተዋል ። በቀን 2,000 ቶን በቆሎ የመፍጨት አቅም ያለው የቡሳ ጎኖፋ የተቀናጀ የምግብ ኢንዱስትሪ ግንባታንም በይፋ አስጀምረዋል ። ቴክኖሎጂ፣ ኢንዱስትሪ እና ማዕድን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕግ ማስከበር ሥራን በቴክኖሎጂ ለማገዝ የሀገሪቱን የመጀመሪያ ሰው አልባ "ስማርት" የፖሊስ አገልግሎት አስጀምረዋል ። በኢንዱስትሪ ዘርፍ የአርጆ የድንጋይ ከሰል ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የጎበኙ ሲሆን፣ ይህም #ኢትዮጵያታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ወደ 66.3 በመቶ ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ይደግፋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመንግሥት እና በግል ባለሀብቶች ጥምረት እየለማ ያለውን የቱሉ ካፒ ወርቅ ልማት ፕሮጀክትንም ጎብኝተዋል። ኢኮ-ቱሪዝም እና ዘላቂ ልማት:- በ"ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በወሎ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሎጎ ሀይቅ ሪዞርትን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። በነቀምቴ ከተማ አቅራቢያ በ14 ሄክታር ላይ በፍጥነት እየተገነባ ያለውን የሶርጋ ኢኮ ሎጅንም ጎብኝተዋል። በተጨማሪም በምሥራቅ ወለጋ የመዴ ጃለላ ቀበሌ የገጠር ኮሪደር ልማት ፕሮጀክትን በመጎብኘት ዘመናዊ የፀሐይ ኃይል እና የባዮ ጋዝ ሥርዓቶች የገጠሩን ማኅበረሰብ ሕይወት እንዴት እየቀየሩ እንደሆነ ተመልክተዋል። ዓለም አቀፋዊ ግንኙነቶች:- በዲፕሎማሲው ረገድ ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የጣሊያን አፍሪካ ጉባዔ ባዘጋጀችበት ወቅት፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጣሊያኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒን የተቀበሉ ሲሆን 39ኛውን የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ሊታደሙ ከመጡ የተለያዩ ሀገራት መሪዎችም ጋር ፍሬያማ የሁለትዮሽ ስብሰባ አድርገው ነበር፡፡ በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቱርክዬን ፕሬዝዳንት ረጀፕ ጣይብ ኤርዶዋንን እና የእስራኤሉን ፕሬዝዳንት ይስሐቅ ሄርዞግን በአዲስ አበባ ተቀብለው ስለ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ቀጣናዊ መረጋጋት ጨምሮ በመጠነ ሰፊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)በአዘርባጃን ባደረጉት ይፋዊ የሥራ ጉብኝትም ከፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ጋር በመሆን የመከላከያ ትብብር ስምምነት፣ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ፣ በኢንቨስትመንት፣ በጸረ-ሙስና እና ሌሎች ዘርፎች ላይ ያተኮሩ የመግባቢያ ሰነዶችን ተፈራርመዋል ። ብሔራዊ ደህንነት እና ተቋማዊ ሪፎርም:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የልዩ ኦፕሬሽን ኮማንድ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ በመገኘት ዘመናዊ የአየር እና የውሃ ላይ ወታደራዊ ትርዒቶችን ተመልክተዋል ። ኮማንዱ ወቅታዊ የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት በሚያስችል መልኩ በዘመናዊ መልክ መዋቀሩን አድንቀዋል። በተጨማሪም የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባን በመምራት በቀጣይ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ የተወያዩ ሲሆን፣ ቀጣዩ ምርጫ ሰላማዊ እና ፍትሃዊ እንዲሆን መንግሥት ቁርጠኛ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጥናት ላይ የተመሰረቱ አማራጮችን ይዘው ሊቀርቡ ይገባል
Mar 3, 2026 79
ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ በመጪው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክንያታዊና በጥናት ላይ የተመሰረተ አማራጮችን ይዘው ሊቀርቡ እንደሚገባ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን አመለከቱ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም ለማካሄድ ቀነ ቀጠሮ መያዙ የሚታወቅ ሲሆን ተወዳዳሪ ፓርቲዎችም ቅስቀሳን ጨምሮ የተለያዩ ቅድመ ምርጫ ዝግጅቶችን እያደረጉ ነው። በጉዳዩ ዙሪያ ኢዜአ ያነጋገራቸው በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን እንዳሉት በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህዝቡን የሚጠቅሙ አማራጭ ሃሳቦችንና ፖሊሲዎችን ይዘው በመቅረብ መወዳደር አለባቸው። በዩኒቨርሲቲው የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እሸቱ ተስፋዬ ምርጫ ዜጎች ዴሞክራሴያዊ መብታቸውን የሚጠቀሙበትና የዴሞክራሴያዊ ስርዓት ማሳያ መሳሪያ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በታሪኳ ለ7ኛ ጊዜ ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆኗን ጠቅሰው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዘላቂነት የህዝብንና የሀገርን ችግር በሚፈቱ ጉዳዮች ላይ ማተኮር ይገባቸዋል ነው ያሉት። በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እንዲሁም በዲፕሎማሲያዊ ዘርፎች ሃሳባቸውን ሸጠው በዴሞክራሴያዊ ስርዓት ግንባታ ላይ ሚናቸውን መወጣት እንደሚገባቸውም አንስተዋል። የቅድመ ምርጫ ወቅት የክርክሮችና ውይይቶች የዴሞክራሲ፣ የስልጣኔ መገለጫዎች መሆናቸውንም ተናግረዋል። ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ግንዛቤ የመፍጠሩ ስራ ትኩረት ሊደረግበት ይገባል ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የሰላምና ደህንነት ትምህርት መምህርና ተመራማሪ ወንድሙ አዴ ናቸው። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለህዝብና ለሀገር የሚበጁ አማራጭ ሀሳቦችን፣ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ይዘው በመቅረብ ማስተዋወቅ እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። በምርጫ ቅስቀሳ እና ክርክር ወቅት በሰለጠነ መንገድ ከተንቀሳቀሱ ህዝቡም ድምጹን እንደሚሰጥ ጠቁመው የምርጫ ህጉንና ዕውቀትን መሠረት ባደረገ መልኩ ክርክሮች ሊደረጉ ይገባል ነው ያሉት።
የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ድጋፋችንን እናጠናክራለን - ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች
Mar 3, 2026 93
ሀዋሳ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ እንዲያገኝ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ታሪካዊ እና ሕጋዊ መሰረት ያለው ከመሆኑም በላይ የሉዓላዊነትና የትውልዱ የሕልውና ጉዳይ ነው። ኢዜአ ያነጋገራቸው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እንዳሉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን በተመለከቱ ጉዳዮች የጋራ አቋም ይዞ መስራት ከሁሉም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ፓርቲ ደቡብ ቀጠና ሲዳማ ክልል ማስተባበሪያ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ ሀረገወይን ዘሪሁን ፓርቲያቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስከብሩ ጉዳዮች ላይ ፅኑ አቋም ይዞ ይሰራል ብለዋል። ብሔራዊ ጥቅምን የሚያሳድጉ ማናቸውም የልማት ሥራዎችና ጥረቶች ለነገው ትውልድ የሚጠቅሙና የሚሻገሩ በመሆናቸው ስኬታማ እንዲሆኑ ፓርቲው የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ነው የገለጹት። የሲዳማ አንድነት ፓርቲ(ሲአፓ) ሊቀ መንበር ለማ ሆያቶ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን ያጣችው በአንድ ወቅት በተፈጠረ ታሪካዊ ስህተትና የፖለቲካ ሴራ ነው፤ በዚህም ላለፉት በርካታ ዓመታት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጉዳት ስናስተናግድ መቆየቷ የሚያስቆጭ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም ጥያቄው ምላሽ እንዲያገኝ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን እስከመጨረሻው ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸውን ነው የሚገልጹት። በብልፅግና ፓርቲ ሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የክልሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ኤርሚያስ ኢትዮጵያ በሴራ ያጣችውን የባሕር በር ለማስመለስ ያለልዩነት መስራት ያስፈልጋል። ኢትዮጵያ አሁን ካላት የህዝብ ቁጥርና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አኳያ የገጠሟትን ተግዳሮቾች ለመፍታት የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የግድ ነው ብለዋል። በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሆነ የምክር ቤቱ አባላት በኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ አቋም መያዛቸውንም ተናግረዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያን የሚገነባት እና የሚያጸናት የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው - አቶ መለሰ ዓለሙ
Mar 4, 2026 27
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ ለሀገራዊ መግባባት በምክክሩ የሚያደርገውን አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል። ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት ተችሏል የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 የተቋቋመው፣ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ መሠረታዊ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት እና በሕዝቦች መካከል የጋራ መግባባትን ለመፍጠር ነው። ኮሚሽኑ አካታች የሆኑ የምክክር መድረኮችን በማመቻቸት ለዘላቂ ሰላም እና ለጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚረዱ ምክረ ሀሳቦችን የማቅረብ ግብም አለው። ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥ በየክልሎቹና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተወካዮች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎችን በስፋት አከናውኗል። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ብልፅግና ፓርቲ ምክክር ኢትዮጵያን ጠንካራ ሀገር ያደርጋታል የሚል ፅኑ እምነት እንዳለው ገልፀዋል። ብልፅግና ፓርቲ በሀገራዊ ምክክር የእስካሁን ሂደት ውስጥ ግልፅ የሆነ አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መቆየቱንም አስታውሰዋል። የምክክር ሂደት ለዘመናት የተሻገረና ከሀገረ መንግስት ግንባታ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በዘመናት መካከል በተለያዩ ምክንያቶች የተፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያን የሚገነባትና የሚያጸናት የኢትዮጵያውያን የተደመረ ፍላጎትና ሀሳብ ነው ያሉት አቶ መለሰ፤ ፓርቲው ምክክርን የአንድ ወገን ሥራ አድርጎ እንደማይመለከተውም ተናግረዋል። ምክክሩ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ መሆኑን በማመን፣ ፓርቲው በውይይት በመሳተፍና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ይበጃሉ ያላቸውን አጀንዳዎች በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። እንደ ገዥ ፓርቲም ሂደቱ እንዲሳካ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን አክለዋል። የምክክር ሂደቱ ለስምንት ወራት መራዘሙ ኮሚሽኑ ሥራውን በአግባቡና በጥራት እንዲያጠናቅቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል። ብልፅግና ፓርቲም በቀጣይ ወራት ለሀገራዊ መግባባት እየተካሄደ ላለው ምክክር አዎንታዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በዚህም ፓርቲው ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ የመግባባት ደረጃ ላይ እንድትደርስ ይሰራል ብለዋል። ብልፅግና ፓርቲ የምክክር ሂደት ለትውልድ የሚኖረውን የላቀ ፋይዳ በሚገባ የሚገነዘብ በመሆኑ አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሁሌም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በትግሪኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ካስተላለፏቸው መልዕክቶች
Mar 3, 2026 98
ለትግራይ ሕዝብና ወጣቶች ያስተላለፉት መልዕክት፡- "የትግራይ ሕዝብ ከጦርነት ይልቅ ሰላምና ልማት ይገባዋል" ብለዋል። ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁ መክረዋል። መንግሥት በትግራይ ክልል ሰላም እንዲሰፍንና ዳግም ጦርነት እንዳይከሰት ጽኑ ፍላጎት እንዳለውና ለዚህም ማንኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል አረጋግጠዋል። የሰሜኑን ጦርነት መንስኤዎች በተመለከተ ህወሓት ከ50 ዓመት በፊት በነበረ ኋላቀር አስተሳሰብ የታሰረ መሆኑና ለውጥን ለመቀበል አለመፈለጉ። ዓለም በቴክኖሎጂና በ"ፕራግማቲዝም" በምትመራበት ዘመን፣ ድርጅቱ በአሮጌው መንገድ ለመጓዝ መሞከሩ ለግጭት ዳርጎታል። ቆሞ ቀሩ ኃይል "ኢትዮጵያ ትፈርሳለች" የሚል የተሳሳተ ስጋት በመዝራት የለውጡን ኃይል እንደ ጠላት ማየቱ። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተግባራዊነት በተመለከተ ፡- መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ሰላም እንዲያገኝ ባንክ፣ መብራትና ቴሌኮም የመሳሰሉ አገልግሎቶችን በፍጥነት እንዲመለሱ ማድረጉን ገልጸዋል። ሆኖም ቆሞ ቀሩ ቡድን ስምምነቱን "መርጦ የመተግበር" ዝንባሌ እያሳየ መሆኑን ተችተዋል። በተለይም ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ውሳኔ አለማክበሩን ጠቅሰዋል። ድርጅቱ ለልማት የተመደበውን በጀት ለጦርነት ዝግጅትና ለታጣቂዎች ቀለብ እየዋለ መሆኑን ገልጸው፣ ይህም በትግራይ ሕዝብ ላይ ተጨማሪ መከራ እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በጦርነቱ ወቅት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ፡- ጦርነት ሁልጊዜም አስከፊ ገጽታ እንዳለው ገልጸው፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የሽግግር ፍትሕ (Transitional Justice) አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ ሂደት ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ በሆነ መንገድ ሊካሄድ እንደሚገባውና ወንጀል የፈጸሙ አካላት በሕግ መጠየቅ እንዳለባቸው ገልጸዋል። የኤርትራ መንግሥት (ሻዕቢያ) ሚና በጦርነቱ ወቅት የኤርትራ ጦር ያደረገው ድጋፍ የሚታወስ መሆኑን ጠቅሰዋል። ሆኖም በጦርነቱ ሂደት የተፈጸሙ ማናቸውም ዓይነት ጥፋቶች፣ ግድያዎችና ዘረፋዎች (በተለይም በአክሱም፣ ዓድዋና ሽሬ አካባቢዎች) የማይቀበሉትና የሚወገዝ ተግባር መሆኑን በግልጽ አስታውቀዋል። መንግሥት ማንኛውንም የውጭ ኃይል ጣልቃ ገብነት እንደሚቃወምና የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር እንደሚሠራ ገልጸዋል።
የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤን የማስቀጠል አባዜ ምክንያት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Mar 3, 2026 73
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው የህወሓት አመራር ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤ የማስቀጠል አባዜ ምክንያት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ ቆይታ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የሰሜኑ ጦርነት መነሻ ምክንያቶችን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፤ ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና እኔ ብቻ በሚል ስሜት በመዋጡ ግጭት እንዲነሳ መንስኤ መሆኑን ገልጸዋል። ህወሓት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብ የታሠረ ድርጅት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ብቻ ሳይሆን ዓይኑን ጨፍኖ ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ ርምጃዎችን ሲወስድ መቆየቱንም ተናግረዋል። የለውጡ ኃይል የጀመረውን ጉዞ ለማደናቀፍ መሞከሩን ገልጸው፤ በህወሓት ቆሞ ቀር አስተሳሰብ የተነሳው ጦርነት ጉዳት ማስከተሉንም አንስተዋል። ሁለተኛው ቁልፍ ምክንያት ደግሞ ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ ጋር የተሣሠረ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ህወሓት ኢትዮጵያ በጥርጣሬና በሥጋት ውስጥ እንድትኖር መስራቱ ለችግሮች መባባስ ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል። ቆሞ ቀሩ ኃይል ከ50 ዓመት በፊት ከነበረው አስተሳሰብ ውጭ ሊንቀሳቀስ አለመቻሉን ጠቅሰው፤ ይህ ደግሞ ከለውጡ ጋር አብሮ ለመሄድ እንዳላስቻለው ገልጸዋል። የለውጥ ኃይሉ ዓለምን ያስደመመ ተአምራዊ ለውጦችን ማምጣቱን ጠቅሰው፤ ቆሞ ቀር ኃይሉ ከለውጥ ኃይሉ ጋር ተስማምቶ ሕዝቡንና ነፍሱን እንደመለወጥ የልማት ሽታ ከማያውቁ ኋላቀሮች ጋር እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ ያለው የፖለቲካ ስብራት ሌላኛው መንስኤ እንደሆነ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተሳሳተ ትርክት ላይ የተመሰረተው ፖለቲካዊ መዋቅር የፖለቲካ ስርዓቱ እንዲበላሽ ማድረጉን ነው ያብራሩት። ጦርነቱ የራሱ ልዩ ገጽታዎች እንዳሉት ሆኖ ከሀገራዊ መዋቅር ችግር የተለየ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባውም ብለዋል። ይህ አዙሪት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መሰበር አለበት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይሄንን ለመስበር ደግሞ ኃላፊነት መውሰድ እንደሚገባ ገልጸዋል። እንደ ትውልድ ይበቃል ብለን መሥራት አለብን ሲሉም ተናግረዋል። የመንግስት አቋም ችግሮችን በውይይት መፍታት አማራጭ የሌለው መንገድ እንደሆነ በጽኑ እንደሚያምንም ገልጸዋል። ይሄንን ለማድረግ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ወሳኝ ሀገራዊ መፍትሔ ሊሆን ይችላል ብለን እናምናለን ብለዋል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ እስካሁን ከሞላ ጎደል ከትግራይ ውጭ አብዛኛው ሥራ እየተገባደደ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በትግራይ ክልል ግን ውይይት እንዳይደረግ፣ ሕዝባችን ቁጭ ብሎ እንዳይወያይ፣ ጥያቄ አንሥቶ መፍትሔ እንዳያገኝ፣ ያ ቆሞ ቀር ኃይል ሆን ብሎ እየሠራ ይገኛል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ደግሞ ትክክለኛ አካሄድ ነው ብዬ አላምንም ብለዋል።
ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት ተችሏል
Mar 3, 2026 96
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ ለተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት የሚጥሉ ጠንካራና ገለልተኛ የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት መገንባት መቻሉን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። ዛሬ "የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት እመርታ፤ ለተሳካ ሀገረ መንግሥት ግንባታ!" በሚል መሪ ሀሳብ በዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት ቅንጅት ላይ የሚያተኩር ሀገራዊ መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምሕረት የፍርድ ቤቶች የለውጥ ተግባራትን አስመልክቶ ባቀረቡት የመነሻ ሐሳብ፤ የዳኝነት ነጻነትን ለማጠናከር የሕግ ማሻሻያ መደረጉን ተናግረዋል። ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ አኳያም ግልጽ ችሎትን የማስፋፋት ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፤ ግልጽ ችሎት ከነበረበት 65 በመቶ ወደ 91 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። ፍርድ ቤቶች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ድምፅን ወደ ጽሁፍ የሚቀይር ቴክኖሎጂን በመጠቀም ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ኮሚሽኑ እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እስካሁን ውጤታማ የሚባሉ ሥራዎችን ሰርቷል ብለዋል። የሀገሪቱን ሁሉንም ክልሎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ 93 በመቶ ማካተት መቻሉን ጠቁመው፤ በቀጣይም አጀንዳ መቅረጽና ይፋ ማድረግ እንዲሁም ሀገራዊ ምክክር ማካሄድ ከሚከናወኑ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ የቦርዱን የለውጥ እና ቀጣይ ተግባራት ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ቦርዱ ባለፉት ዓመታት ተቋማዊ የሕግ ማሻሻያዎችን በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የዕጩዎችን ምዝገባ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል በማከናወን ማጠናቀቅ መቻሉን ተናግረው፤ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ስልጠና መሰጠት መቻሉንም ገልጸዋል። ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬታማነት ለማከናወን "ምርጫዬ" የመራጮች መመዝገቢያ የዲጂታል አማራጭ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ባቀረቡት የመነሻ ጽሑፍ፤ ነጻና ገለልተኛ ተቋም ለመገንባት የአዋጅ ማሻሻያ፣ ደንብና መመሪያዎችን ማሻሻል መቻሉን ገልጸዋል። ከኦዲት ሽፋን አኳያም የፋይናንሻል ኦዲት መቶ በመቶ ማከናወን መቻሉን በመጥቀስ፤ የክዋኔ ኦዲትንም ከ24 ወደ 41 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል። የኢትየጵያ ሕዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕምባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ ከለውጡ ወዲህ በተከናወኑ የለውጥ ስራዎችም ከአሰራርና ከሰው ሃይል አኳያ፣ የሕግ ማሻሻያ ተግባራት፣ ከቴክኖሎጂ አኳያ እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራሮች ተዘርግተው ስኬታማ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። ከቴክኖሎጂ ስራዎች ለግልጸኝነት፣ ለተጠያቂነት፣ ለቅልጥፍና እንዲሁም ለውጤታማነት ምቹ መደላድል መፍጠራቸውን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ባቀረቡት የመነሻ ጽሑፍ፤ ከለውጡ በፊት ኮሚሽኑ ገለልተኛ እና ውጤታማ ያልነበረ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ምቹ የሕግ ማዕቀፍ፣ አዲስ የሰው ሃብት መዋቅር፣ ብቃትና አቅም ያለው አመራር መፍጠር፣ ሥራን የሚያቀላጥፉ በቴክኖሎጂ የተደገፉ መፍትሔዎች፣ የመረጃ ስርዓት በቴክኖሎጂ የሚመራ መደረጉ እንዲሁም የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ መቻሉን ጠቁመዋል። የመድረኩ ታሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉን አድንቀዋል፡፡ ይህም ለሀገረ መንግስት ግንባታ ብሎም ለዘላቂ ልማትና ለሕዝቦች ተጠቃሚነት መረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በሰጡት ማጠቃለያ፤ ለምክር ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት በሕግ የተሰጣቸውን ሥልጣንና ኃላፊነት በገለልተኝነትና በነፃነት እየተወጡ ይገኛሉ። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዳኝነትና ዲሞክራሲ ተቋማት ላይ መሠረታዊ የሪፎርም ሥራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። ተቋማቱ ላይ ከተከናወኑ የለውጡ ስራዎች መካከል የማቋቋሚያ አዋጆቻቸውን በድጋሚ መፈተሽና ማሻሻል፣ የአመራር ሥርዓታቸውን ይበልጥ ውጤታማ ማድረግ፣ ዘመናዊና ግልጽነት ያለው የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት መቻል ዋና ዋናዎቹ ናቸው ብለዋል፡፡ የተቋማት ግንባታ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ ነው ያሉት አፈ-ጉባኤው፤ ተቋማቱ ነፃ ሆነው እንዲሠሩ መደረጉ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና ዴሞክራሲን እውን ለማድረግ ትልቅ መሠረት እንደሚጥል አጽንኦት ሰጥተዋል። ተቋማቱ በገለልተኝነት መሥራታቸው ጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን ለማፋጠን ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም ጠቁመዋል።
የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) ከአፍሪካ ሀገራት የመከላከያ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ
Mar 3, 2026 85
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) ከአፍሪካ ሀገራት የመከላከያ ሚኒስትሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ የተደረገው 130ኛው የዓድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች ኮንፈረንስ ጎን ለጎን ነው። የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ከመጡ የመከላከያ ሚኒስትሮችና የልዑካን ቡድን መሪዎች ጋር ውጤታማ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ማድረጋቸውን ኢዜአ ከመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ወቅት ቀደም ሲል በሀገራቱ መካከል የተፈረሙ የትብብር ስምምነቶች ያሉበት የአፈፃፀም ደረጃ በጥልቀት የተገመገመ ሲሆን፣ በቀጣይም ትብብሩን ይበልጥ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ አዳዲስ የመግባቢያ ሰነዶችን ጨምሮ በልዩ ልዩ የሥራ መስኮች ላይ በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ተደርሷል። ሚኒስትሯ በውይይቱ ወቅት እንደገለፁት፤ የዓድዋ ድል ከታሪካዊ ፋይዳው ባሻገር ዛሬ አፍሪካ ከፊቷ የተደቀኑባትን ወቅታዊ የፀጥታና የደኅንነት ስጋቶች በጋራ ለመመከት እንደ ትልቅ የመንፈስ ምንጭና የትብብር ማዕቀፍ ሊያገለግል ይገባል። በመሆኑም የአህጉሪቱን ሰላምና መረጋጋት ለማረጋገጥ የሚያስችል የጋራ ግንዛቤ በመያዝ፣ በአንድነትና በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። በተለይም በወታደራዊ ቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሥልጠናና በልምድ ልውውጥ መስኮች በጋራ ለመሥራት መግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን፣ ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ የፀጥታ ስጋቶችን በጋራ ለመከላከል የሚያስችሉ ስልታዊ የትብብር አቅጣጫዎችም ተቀምጠዋል። በውይይቱ የተሳተፉት የአፍሪካ ሀገራት የመከላከያ ሚኒስትሮች በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ለአህጉራዊ ሰላምና መረጋጋት እያበረከተች ያለውን ቀዳሚና የማይተካ ሚና አድንቀዋል። የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነውን የዓድዋ ድል በዓልን በኢትዮጵያ ተገኝተው ከወንድሞቻቸው ጋር በጋራ በማክበራቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ደስታ ገልፀው፣ በቀጣይም በጋራ የመከላከል አቅም ግንባታ ላይ በቁርጠኝነት ለመሥራት ያላቸውን ፅኑ ፍላጎት አረጋግጠዋል። የሁለትዮሽ ውይይቱ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነት ከማሳደጉም ባለፈ፣ የአህጉሪቱን የጋራ ደኅንነትና ትስስር ለማረጋገጥ የሚደረገውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል። ሚኒስትሯ ውይይት ካደረጉባቸው ሀገራትና ተቋማት መካከል የኬንያ፣ የደቡብ ሱዳን፣ የዚምባብዌ፣ የዛምቢያ፣ የኮንጎ ሪፐብሊክ ፣የቦትስዋና፣ የሩዋንዳ፣ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ የካሜሩን፣ የማሊ እና የአልጄሪያ የመከላከያ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ ጄኔራሎች እንዲሁም የምሥራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ይገኙበታል።
የወርሃ ጥር እና የካቲት 𝟐𝟎𝟏𝟖 የስራ ትግበራዎች ማጠቃለያ
Mar 3, 2026 126
በሁለቱ ወራት ፈር ቀዳጅ የዲጂታል አገልግሎቶች፣ መጠነ ሰፊ የመሠረተ ልማት እና የኢኮ-ቱሪዝም ልማቶች የተመረቁበት እንዲሁም ስትራቴጂካዊ ዓለም አቀፍ ትብብሮች የተጠናከሩበት ነበር። የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ𝟔ኛው የሥራ ዘመን 𝟏𝟎ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ የኢኮኖሚ እና ፖለቲካዊ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከአባላቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ኢትዮጵያ በዓመቱ መጨረሻ የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ጠቁመዋል። በሪፎርሙ ማግስት መንግሥት አንድም የንግድ ብድር ባለመውሰዱ የሀገሪቱን የዕዳ ጫና መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል። ባለፉት ስድስት ወራት ከሸቀጥ ኤክስፖርት 5.1 ቢሊዮን ዶላር (የዕቅዱን 120 በመቶ)፣ ከአገልግሎት ዘርፍ 4.5 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም ከሬሚታንስ 4.6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ይፋ አድርገዋል። በቴክኖሎጂ ረገድም የአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ኢንስቲትዩት መቋቋሙን እና በዓለም ሁለተኛ የሆነው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ሊከፈት መሆኑን፣ የሞባይል ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን እንዲሁም የሞባይል ገንዘብ ተጠቃሚዎች 58 ሚሊዮን መድረሳቸውን ገልጸዋል። ብሔራዊ ሰላምን በተመለከተ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት እንደሚገባ፣ የወልቃይት ነዋሪዎች በሰላም የመኖር መብት እንዳላቸው እና የትግራይ ሕዝብ በፖለቲካው መድረክ ዋና ተዋናይ መሆን እንዳለበት አሳስበዋል ። መሠረተ ልማት እና የከተማ ትራንስፎርሜሽን:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መጠነ ሰፊ የመሠረተ ልማት ክንውኖችን በመጎብኘት እና በማስጀመር የሀገሪቱን የዘመናዊነት ጉዞ በተግባር ያረጋገጡበት ወር ነበር። በሀዋሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ የተመለከቱ ሲሆን፣ በነቀምቴ ከተማም ዘመናዊ የትራፊክ አስተዳደር እና ከመሬት በታች የሚዘረጉ የመሠረተ ልማት ሥርዓቶችን ያካተተውን የኮሪደር ልማት ሥራ ጎብኝተዋል ። ግብርና፣ መስኖ እና የምግብ ሉዓላዊነት:- የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዋና ዋና የግብርና ስፍራዎች የመስክ ምልከታ አድርገዋል። በ"ሌማት ትሩፋት" መርሐ ግብር በሀዋ ገላን ወረዳ የለማውን የሙዝ ክላስተር የጎበኙ ሲሆን፣ ለተለያዩ ሰብሎች አስተማማኝ የውሃ አቅርቦት የሚሰጠውን የቄጦ መስኖ መሠረተ ልማት ፕሮጀክትንም ተመልክተዋል ። በተጨማሪም የአርጆ ዲዴሳ መስኖ ፕሮጀክት ያለበትን ደረጃ የገመገሙ ሲሆን፣ በብላቴ ወንዝ አካባቢ በግል ባለሀብቶች እየለሙ ያሉ የፍራፍሬ ልማቶችን ጎብኝተዋል ። በቀን 2,000 ቶን በቆሎ የመፍጨት አቅም ያለው የቡሳ ጎኖፋ የተቀናጀ የምግብ ኢንዱስትሪ ግንባታንም በይፋ አስጀምረዋል ። ቴክኖሎጂ፣ ኢንዱስትሪ እና ማዕድን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕግ ማስከበር ሥራን በቴክኖሎጂ ለማገዝ የሀገሪቱን የመጀመሪያ ሰው አልባ "ስማርት" የፖሊስ አገልግሎት አስጀምረዋል ። በኢንዱስትሪ ዘርፍ የአርጆ የድንጋይ ከሰል ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የጎበኙ ሲሆን፣ ይህም #ኢትዮጵያታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ወደ 66.3 በመቶ ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ይደግፋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመንግሥት እና በግል ባለሀብቶች ጥምረት እየለማ ያለውን የቱሉ ካፒ ወርቅ ልማት ፕሮጀክትንም ጎብኝተዋል። ኢኮ-ቱሪዝም እና ዘላቂ ልማት:- በ"ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በወሎ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሎጎ ሀይቅ ሪዞርትን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። በነቀምቴ ከተማ አቅራቢያ በ14 ሄክታር ላይ በፍጥነት እየተገነባ ያለውን የሶርጋ ኢኮ ሎጅንም ጎብኝተዋል። በተጨማሪም በምሥራቅ ወለጋ የመዴ ጃለላ ቀበሌ የገጠር ኮሪደር ልማት ፕሮጀክትን በመጎብኘት ዘመናዊ የፀሐይ ኃይል እና የባዮ ጋዝ ሥርዓቶች የገጠሩን ማኅበረሰብ ሕይወት እንዴት እየቀየሩ እንደሆነ ተመልክተዋል። ዓለም አቀፋዊ ግንኙነቶች:- በዲፕሎማሲው ረገድ ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የጣሊያን አፍሪካ ጉባዔ ባዘጋጀችበት ወቅት፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጣሊያኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒን የተቀበሉ ሲሆን 39ኛውን የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ሊታደሙ ከመጡ የተለያዩ ሀገራት መሪዎችም ጋር ፍሬያማ የሁለትዮሽ ስብሰባ አድርገው ነበር፡፡ በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቱርክዬን ፕሬዝዳንት ረጀፕ ጣይብ ኤርዶዋንን እና የእስራኤሉን ፕሬዝዳንት ይስሐቅ ሄርዞግን በአዲስ አበባ ተቀብለው ስለ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ቀጣናዊ መረጋጋት ጨምሮ በመጠነ ሰፊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)በአዘርባጃን ባደረጉት ይፋዊ የሥራ ጉብኝትም ከፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ጋር በመሆን የመከላከያ ትብብር ስምምነት፣ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ፣ በኢንቨስትመንት፣ በጸረ-ሙስና እና ሌሎች ዘርፎች ላይ ያተኮሩ የመግባቢያ ሰነዶችን ተፈራርመዋል ። ብሔራዊ ደህንነት እና ተቋማዊ ሪፎርም:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የልዩ ኦፕሬሽን ኮማንድ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ በመገኘት ዘመናዊ የአየር እና የውሃ ላይ ወታደራዊ ትርዒቶችን ተመልክተዋል ። ኮማንዱ ወቅታዊ የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት በሚያስችል መልኩ በዘመናዊ መልክ መዋቀሩን አድንቀዋል። በተጨማሪም የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባን በመምራት በቀጣይ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ የተወያዩ ሲሆን፣ ቀጣዩ ምርጫ ሰላማዊ እና ፍትሃዊ እንዲሆን መንግሥት ቁርጠኛ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጥናት ላይ የተመሰረቱ አማራጮችን ይዘው ሊቀርቡ ይገባል
Mar 3, 2026 79
ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ በመጪው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክንያታዊና በጥናት ላይ የተመሰረተ አማራጮችን ይዘው ሊቀርቡ እንደሚገባ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን አመለከቱ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም ለማካሄድ ቀነ ቀጠሮ መያዙ የሚታወቅ ሲሆን ተወዳዳሪ ፓርቲዎችም ቅስቀሳን ጨምሮ የተለያዩ ቅድመ ምርጫ ዝግጅቶችን እያደረጉ ነው። በጉዳዩ ዙሪያ ኢዜአ ያነጋገራቸው በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን እንዳሉት በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህዝቡን የሚጠቅሙ አማራጭ ሃሳቦችንና ፖሊሲዎችን ይዘው በመቅረብ መወዳደር አለባቸው። በዩኒቨርሲቲው የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እሸቱ ተስፋዬ ምርጫ ዜጎች ዴሞክራሴያዊ መብታቸውን የሚጠቀሙበትና የዴሞክራሴያዊ ስርዓት ማሳያ መሳሪያ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በታሪኳ ለ7ኛ ጊዜ ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆኗን ጠቅሰው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዘላቂነት የህዝብንና የሀገርን ችግር በሚፈቱ ጉዳዮች ላይ ማተኮር ይገባቸዋል ነው ያሉት። በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እንዲሁም በዲፕሎማሲያዊ ዘርፎች ሃሳባቸውን ሸጠው በዴሞክራሴያዊ ስርዓት ግንባታ ላይ ሚናቸውን መወጣት እንደሚገባቸውም አንስተዋል። የቅድመ ምርጫ ወቅት የክርክሮችና ውይይቶች የዴሞክራሲ፣ የስልጣኔ መገለጫዎች መሆናቸውንም ተናግረዋል። ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ግንዛቤ የመፍጠሩ ስራ ትኩረት ሊደረግበት ይገባል ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የሰላምና ደህንነት ትምህርት መምህርና ተመራማሪ ወንድሙ አዴ ናቸው። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለህዝብና ለሀገር የሚበጁ አማራጭ ሀሳቦችን፣ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ይዘው በመቅረብ ማስተዋወቅ እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። በምርጫ ቅስቀሳ እና ክርክር ወቅት በሰለጠነ መንገድ ከተንቀሳቀሱ ህዝቡም ድምጹን እንደሚሰጥ ጠቁመው የምርጫ ህጉንና ዕውቀትን መሠረት ባደረገ መልኩ ክርክሮች ሊደረጉ ይገባል ነው ያሉት።
የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ድጋፋችንን እናጠናክራለን - ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች
Mar 3, 2026 93
ሀዋሳ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ እንዲያገኝ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ። የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ታሪካዊ እና ሕጋዊ መሰረት ያለው ከመሆኑም በላይ የሉዓላዊነትና የትውልዱ የሕልውና ጉዳይ ነው። ኢዜአ ያነጋገራቸው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እንዳሉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን በተመለከቱ ጉዳዮች የጋራ አቋም ይዞ መስራት ከሁሉም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ፓርቲ ደቡብ ቀጠና ሲዳማ ክልል ማስተባበሪያ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ ሀረገወይን ዘሪሁን ፓርቲያቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስከብሩ ጉዳዮች ላይ ፅኑ አቋም ይዞ ይሰራል ብለዋል። ብሔራዊ ጥቅምን የሚያሳድጉ ማናቸውም የልማት ሥራዎችና ጥረቶች ለነገው ትውልድ የሚጠቅሙና የሚሻገሩ በመሆናቸው ስኬታማ እንዲሆኑ ፓርቲው የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ነው የገለጹት። የሲዳማ አንድነት ፓርቲ(ሲአፓ) ሊቀ መንበር ለማ ሆያቶ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን ያጣችው በአንድ ወቅት በተፈጠረ ታሪካዊ ስህተትና የፖለቲካ ሴራ ነው፤ በዚህም ላለፉት በርካታ ዓመታት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጉዳት ስናስተናግድ መቆየቷ የሚያስቆጭ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም ጥያቄው ምላሽ እንዲያገኝ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን እስከመጨረሻው ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸውን ነው የሚገልጹት። በብልፅግና ፓርቲ ሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የክልሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ኤርሚያስ ኢትዮጵያ በሴራ ያጣችውን የባሕር በር ለማስመለስ ያለልዩነት መስራት ያስፈልጋል። ኢትዮጵያ አሁን ካላት የህዝብ ቁጥርና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አኳያ የገጠሟትን ተግዳሮቾች ለመፍታት የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የግድ ነው ብለዋል። በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሆነ የምክር ቤቱ አባላት በኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ አቋም መያዛቸውንም ተናግረዋል።
ማህበራዊ
የፍትሕ ሥርዓት ሪፎርም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በልማትና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ገንቢ ሚና እንዲወጡ እያደረገ ነው
Mar 3, 2026 272
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦የፍትሕ ሥርዓቱ ሪፎርም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በልማትና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ገንቢ ሚና የሚወጡበትን አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያ ሥላሴ ገለጹ። አምስተኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት "ራስን መቻል፤ ለዘላቂ ሰላምና ለአካታች ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ከየካቲት 26 እስከ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል። በዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት ቅንጅት ላይ የሚያተኩር ሀገራዊ መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያ ሥላሴ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የተወሰዱ የሕግና የአሰራር ማሻሻያዎች በሲቪክ ምኅዳሩ ላይ አስቻይ ሁኔታን ፈጥሯል። በዚህም ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሰላም፣ በልማትና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚኖራቸውን ሚና በማሳደግ በነፃነት ተደራጅተው የሚሰሩበት ምኅዳር መፍጠር መቻሉን አስታውቀዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ቁጥር 1113/2011 ዓ.ም የመደራጀት ነፃነትና መብትን የሚያጎናጽፍ ምኅዳር መፍጠር ያስቻለ የአሰራር ሥርዓት እንደሆነም ተናግረዋል። በኢፌዴሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን በተካሄደው የሪፎርም እርምጃም ለመደራጀት መብት ምቹ መደላድልን በመፍጠር መሠረታዊ ለውጥ መምጣቱን ገልጸዋል። ይህም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከዚህ ቀደም ይታዩበት የነበረውን ቁጥጥርን ማዕከል ያደረገ ዕይታ በመቀየር መደራጀት ለሚሹ ዜጎች አስቻይ የስራ ምኅዳር መፍጠሩን አንስተዋል። ከሀገራዊ ለውጡ በፊት በሕገ-መንግስቱ የተቀመጠውን የመደራጀት መብትና ነፃነት የሚቃረኑ አሰራሮች እንደነበሩ ያስታወሱት ሚኒስትሯ፤ አዋጁ መተግበሩም የማህበረሰብ ድርጅቶችን የአሰራር ዕይታ ቀይሯል ብለዋል። በፌዴራል ደረጃ የተደረገው የሕግና የአሰራር ማሻሻያም በክልሎች ጭምር ክትትል በማድረግ በርካታ አዳዲስ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ወደስራ የገቡበትን ዕድል እንደፈጠረም አንስተዋል። በዚህም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ሰላምና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እንዲሁም በተለያዩ የልማት መስኮች የሥራ አድማሳቸውን የሚያሰፉበት አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን አስረድተዋል። ለአብነትም በ2013 ዓ.ም ጠቅላላ ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የተጫወቱት ገንቢ ሚና ተጠቃሽ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስተዋጽኦ መሆኑን አስታውሰዋል። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬትም በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚሰሩ ድርጅቶች ካለፈው ምርጫ ካገኙት ተሞክሮ በመነሳት ገንቢ ሚና ይወጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። ይህም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የነበረባቸውን አሳሪ የሕግና የአሰራር ሥርዓት ለማሻሻል የተወሰዱ እርምጃዎች ውጤታማነት ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል። በየዓመቱ የሚካሄደው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንትም የመንግስትና ባለድርሻ አካላትን ትብብርና አጋርነት በማጠናከር የልምድና ተሞክሮ ልውውጥ የሚደረግበት ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ዘንድሮም ከየካቲት 26 እስከ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ አምስተኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት "ራስን መቻል፤ ለዘላቂ ሰላምና ለአካታች ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በሚካሄደው መድረክም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ የመንግስት ተወካዮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንቱም የመንግስትና ባለድርሻ አካላትን ትብብር፣ ቅንጅትና ትስስር በማጠናከር የተሻለ የልምድ ልውውጥ፣ የፖሊሲና የተግባር ግብዓቶችን ለማቅረብ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የአፈጣጠር ችግር ያለባቸውን ሕፃናት የሕክምና ተደራሽነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተደርጓል
Mar 3, 2026 143
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦የአፈጣጠር ችግር ያለባቸውን ሕፃናት የሕክምና ተደራሽነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ አስታወቁ። በአማራ ክልል የማይበገር የጤና ሥርዓት ለመገንባት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ውጤት እያመጡ ነው "የላቀ ተደራሽነትን ለኢትዮጵያ ልጆች፤ በመከላከል፣ በሕክምና እና በማካተት እናረጋግጥ" በሚል መሪ ሀሳብ፣ ሀገር አቀፍ የአፈጣጠር ችግር የሕክምና አገልግሎት ሳምንት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የአፈጣጠር ችግርን ለመከላከል ሕፃናት ከመፈጠራቸው በፊት እና በእርግዝና ወቅት የሚደረጉ ጥንቃቄዎች ወሳኝ መሆናቸውን አስታውቀዋል። እናቶች ከመፀነሳቸው በፊት እና በእርግዝና ወቅት የፎሊክ አሲድ ንጥረ ነገርን እንዲወስዱ ማስተማር እንዲሁም አመጋገብ ችግርን ቀድሞ ለመከላከል ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ መንግስት ግንዛቤ ከመፍጠር ጀምሮ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝና ይህንንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በተጨማሪም ሕፃናት እንደተወለዱ ችግሮቻቸውን በፍጥነት በመለየት አስፈላጊውን የቀዶ ሕክምና እና ሌሎች ወቅታዊ የሕክምና እርዳታ እንዲያገኙ ማድረግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። አገልግሎቱን በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች ለማጠናከርና የባለሙያዎችን አቅም ለመገንባት የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ዶክተር ደረጀ ገልጸዋል። ሚኒስትር ዴኤታው የአፈጣጠር ችግር ያለባቸው ሕፃናት እንደ ማንኛውም እኩያዎቻቸው ትምህርት ቤት እንዲገቡና እኩል ዕድል እንዲያገኙ ማድረግ የመላው ማኅበረሰብ ኃላፊነት መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል። በጤና ሚኒስቴር የስፔሻሊቲ እና ተሀድሶ አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ ኤርሚያስ ሙላቱ በበኩላቸው፤ በችግሩ ዙሪያ ሰፊ የማኅበረሰብ ግንዛቤ የመፍጠርና ህክምና የመስጠት ስራ ባለፉት አመታት በትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ሀገር አቀፍ የአፈጣጠር ችግር የሕክምና አገልግሎት ሳምንት ተከትሎ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የግንዛቤ እንዲሁም የሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥም አመልክተዋል። ይህ በየዓመቱ የሚከናወነው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት፣ በአፈጣጠር ችግር ዙሪያ ያለውን የተሳሳተ አመለካከት ለመቀየርና ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት ቅንጅት ላይ የሚያተኩር ሀገራዊ መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ
Mar 3, 2026 104
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ በዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት ቅንጅት ላይ የሚያተኩር ሀገራዊ መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። መድረኩ "የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት እመርታ፤ ለተሳካ ሀገረ መንግሥት ግንባታ!" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ነው። የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል በመድረኩ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምሕረት፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት፣ ሚኒስትሮች፣ የዴሞክራሲ ተቋማት አመራሮች፣ የፍትህ አካላት፣ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። መድረኩ በዋናነት በሀገሪቱ የፍትህ ሥርዓት እና በዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ያላቸው ተቋማት ካለፉት ዓመታት ተሞክሮ በመነሳት በቀጣይ ጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ በሚያረጋግጡባቸው ጉዳዮች ላይ በዝርዝር እንደሚመክር ተገልጿል። እንዲሁም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፣ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት፣ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እንዲሁም የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ያስመዘገቧቸው ውጤቶች ቀርበው ውይይት ይካሄድባቸዋል። እነዚህ ተቋማት ከሀገራዊ ለውጡ በፊት የነበሩባቸውን ዘርፈ ብዙ ተግዳሮቶች፣ ከለውጡ ወዲህ ያስመዘገቧቸውን ስኬቶችና ያጋጠሟቸውን እንቅፋቶች በመለየት የቀጣይ የጋራ የሥራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎም ይጠበቃል። የፍትህ አካላት ገለልተኝነትና የዴሞክራሲ ተቋማት ጥንካሬ የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ለማስከበር ወሳኝ መሆናቸው ተመላክቷል። የተቋማቱን የሥራ ቅንጅት ማጠናከር ለሀገራዊ ሪፎርሙ ስኬታማነትና ለተቀናጀ የሀገር ግንባታ ሂደት ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል። ተቋማቱ ያላቸውን ጥንካሬና ድክመት በመገምገም በገለልተኝነትና በብቃት ሕዝባዊ አደራቸውን እንዲወጡ የሚያስችል የጋራ ግንዛቤ መፍጠር የመድረኩ ዋነኛ ግብ መሆኑም ተገልጿል።
በሸገር ከተማ የጤና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያመጡ ነው
Mar 3, 2026 98
ሸገር፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦በሸገር ከተማ የጤና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያመጡ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ጤና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። የከተማው ጤና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ቦቶሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከተማው በጤናው ዘርፍ ይታዩ የነበሩ የፍትሃዊ ተደራሽነት፣ የግብዓት አቅርቦት፣ የፋይናንስ አጠቃቀምና የዲጂታላይዜሽን ክፍተቶች በጥናት ተለይተው ወደ ሥራ ተገብቷል። በዚህም ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የሰለጠነ የሰው ኃይል የማሟላትና ዘመናዊ የላቦራቶሪ መሣሪያዎችን የመትከል ሥራ በሰፊው ተከናውኗል። በተለይም የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሻሻል በተሰራው ሥራ ከጤና ጣቢያዎች በተጨማሪ የማህበረሰብ ፋርማሲዎችን በማስፋፋት፣ ሕብረተሰቡ መድኃኒት በተመጣጣኝ ዋጋ በቅርብ እንዲያገኝ መደረጉን አቶ አበራ ገልጸዋል። የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር በመጨመርም የአገልግሎቱ ተደራሽነት እንዲሰፋ መደረጉን አክለዋል። በኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ የቱሉ ዲምቱ ጤና ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ በቀለ ጦጦው በበኩላቸው፤ ጤና ጣቢያው የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስፈልገውን መድኃኒት፣ የሕክምና ቁሳቁስና የሰው ኃይል ማሟላቱን ገልጸዋል። በተለይም ለእናቶችና ሕፃናት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ፤ ወላድ እናቶችን ከቅድመ ወሊድ እስከ ድህረ ወሊድ ያለውን ክትትል በቴክኖሎጂ በመታገዝ በብቃት እያገለገሉ መሆኑን ተናግረዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የቱሉ ዲምቱ ጤና ጣቢያ ተገልጋዮች በበኩላቸው፤ በሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሠረታዊ ለውጥ ማየታቸውን ገልጸዋል። ከተገልጋዮቹ መካከል አቶ ሀብታሙ ዲታ፤ በጤና ጣቢያው የአገልግሎት አሰጣጡ በየጊዜው እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሰዋል። ''ባለቤቴ በዚሁ ጤና ጣቢያ የወሊድ ክትትል ስታደርግ ቆይታ፤ በወሊድ ሂደቱም የተሻለ አገልግሎት አግኝታለች'' ብለዋል። ሌላዋ ተገልጋይ ወይዘሮ ኢትዮጵያ ጎጎላ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል የነበሩ የአገልግሎት ክፍተቶች በመቃለላቸው በአሁኑ ወቅት የተሟላ ሕክምና በቅርብ እያገኙ መሆኑን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
ኢኮኖሚ
ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚደረገው ዘርፈ ብዙ ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Mar 4, 2026 12
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እያደረገ ያለውን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ገለፁ። በኢትዮጵያ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ሂደት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ነው የብሄራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ካውንስል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በሸገር፣ በቢሾፍቱ እና በአዳማ ከተሞች በሚገኙ ልዩ ልዩ አምራች ኢንዱስትሪዎች በመገኘት የመስክ ምልከታ አድርገዋል። የመስክ ምልከታው በኢንዱስትሪዎች አካባቢ ያሉ ማነቆዎችን በቅርበት ለመረዳትና በካውንስሉ አማካኝነት ፈጣን መፍትሄ ለመስጠት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል። የካውንስሉ አባል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባንኩ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እያደረገ ያለውን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል። ባንኩ በዘርፉ ያሉ እውነተኛ ችግሮችን በመለየት በፋይናንስና በውጭ ምንዛሬ በኩል የሚጠበቅበትን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሚሰጠው አጠቃላይ ብድር ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የያዘው የኢንዱስትሪ ፋይናንስ እንደሆነ ነው ፕሬዝዳንቱ የተናገሩት። ከባንኩ የብድር ሴግሜንቶች መካከል ከ45 በመቶ በላይ የሚሆነው ለአምራች ኢንዱስትሪው የቀረበ መሆኑንም ገልጸዋል። አምራች ድርጅቶች አሁንም ተጨማሪ የፋይናንስ አቅርቦት እንደሚፈልጉ የገለጹት አቶ አቤ ሳኖ፣ ባንኩ ይህንን ፍላጎት ለመሙላት ትኩረት መስጠቱን ጠቁመዋል። አጠቃላይ የፋይናንስ አቅምን ማሳደግ ይፈልጋል፤ እኛም የተሻለ ትኩረት ማድረግ እንዳለብን ተረድተናል ሲሉም ፕሬዚዳንቱ አረጋግጠዋል።
የትግራይ ሕዝብ ሰላምና ልማት ይገባዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Mar 3, 2026 67
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ሕዝብ ሰላምና ልማት ይገባዋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ መሆኑን ጠቁመው፤ የሰላም እና ልማት ፍላጎቱ ትልቅ መሆኑንም ገልጸዋል። የትግራይ ክልል ዕረፍት ይፈልጋል፤ ሰላም ይፈልጋል፤ ልማት ይፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል። ክልሉ በሁሉም ክልሎች እየመጣ ያለው ልማትና ሰላም እንደሚገባው ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ ደግሞ በአረጀ አስተሳሰብ ሊረጋገጥ አይችልም ብለዋል። በእርጅናቸው ጊዜ ጦርነት የሚቀሰቅሱትን ደግሞ ተዉ ሊባሉ እና የሀገራችንን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። መንግስት የህዝቡን ፍላጎት ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑንም ነው ጨምረው የገለጹት። ከሰላም ፈላጊዎች ጋር፤ ከተማሩ ወጣቶች ጋር ተባብረን ለትግራይ ክልል ሰላምና ልማት እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በክልሉ የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎችን ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ውጤት እያስገኘ ነው
Mar 3, 2026 140
ሀዋሳ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎችን ውጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተጀመረው ሥራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡ የክልሉ የሥራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት የሰባት ወራት የሥራ አፈጻጻም ግምገማ ተካሂዷል። በለውጡ ዓመታት በሸበሌ ዞን፣ ጎዴ እና ደገሃቡር ከተሞች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እንደገለጹት፡ ባለፉት ሰባት ወራት በሥራ ዕድል ፈጠራ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው፡፡ በበጀት ዓሙቱ ለ71 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱን ያስታወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ በእስካሁን ሂደት ለ 55 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ የክልሉ መንግስት የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸውን ዜጎች ውጤታማ ለማድረግ ከስልጠና ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የጀመረው ሥራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎች በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ አጫጭር ስልጠናዎች ከመስጠት ባለፈ ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ በቀሪ ወራትም ለክልሉ ወጣቶች የመሸጫና የማምረቻ ቦታዎችን እንዲሁም የገንዘብ ብድር በማመቻቸት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ ነው ያስታወቁት። የክልሉ ሥራ፣ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረፅዮን አበበ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ሥራ የተፈጠረላቸውን ዜጎች ውጤታማ ለማድረግ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ከተለመደው አሰራር በመውጣት ባለድርሻ አካላት የሥራ ዕድል ፈጠራን በባለቤትነት እንዲመሩ በመደረጉ የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎችን የሀብት ባለቤት በማድረግ ረገድ አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ በክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቷል ያሉት ደግሞ የቢሮው ምክትልና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ከፍያለው ከበደ ናቸው፡፡ በዚህም ወደስራ ለሚገቡ ወጣቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ስልጠናና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፣ ከ4ሺህ 400 በላይ ዜጎችም የውጭ ሃገር የሥራ ስምሪት አግኝተዋል ብለዋል። በክልሉ ከተፈጠረው የሥራ ዕድል 60 በመቶ የሚሆነው በግብርና ዘርፍ መሆኑን የገለጹት ምክትል ቢሮ ሃላፊው፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎችና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በርካታ ወጣቶች ተሰማርተዋል ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ለነባር ኢንተርፕራይዞች የስልጠና፣ የብድር፣ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ድጋፍ ከመደረጉ በተጨማሪ የገበያ ትስስር በመፍጠር አቅማቸውን የማሳደግ ሥራ መሰራቱንም ተናግረዋል፡፡ በመድረኩ ከክልል እስከ ወረዳ ባሉ መዋቅሮች የተውጣጡ የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡
አስተዳደሩ የህብረተሰቡን የመኖሪያ ቤት ችግር ለማቃለል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው
Mar 3, 2026 186
አምቦ ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦የአምቦ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰቡን የመኖሪያ ቤት ችግር ለማቃለል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገለጸ፡፡ በአምቦ ከተማ ያለውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለማቃለል በማህበር ለተደራጁ 1 ሺህ 516 ነዋሪዎች የቤት መስሪያ ቦታ ተሰጥቷል። ለከተማው ነዋሪዎች ዛሬ የቤት መስሪያ ቦታ የተሰጠው በከተማው ማዘጋጃ ቤት በተከናወነ እጣ የማውጣት መርሀግብር ነው። በሸገር ከተማ የጤና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያመጡ ነው የቦታ ርክክብ መርሀግብሩ ላይ የተገኙት የአምቦ ከተማ ከንቲባ ሃጫሉ ገመቹ እንደገለጹት፤ የቤት መስሪያ ቦታ የተሰጠው በከተማዋ ያለውን የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ ነው። የቤት መስሪያ ቦታ መሰጠቱ በነዋሪዎች ዘንድ ሲነሳ የነበረን ቅሬታ እንደሚያቃልል ገልጸው፣ በበጀት ዓመቱ የቤት መሰሪያ ቦታ ከተሰጣቸው ነዋሪዎች መካከል አብዛኞቹ የመንግስት ሠራተኞች ናቸው ብለዋል። ነዋሪዎቹ በከተማዋ ማስተር ፕላን መሰረት ደረጃውን የጠበቀ ቤት መስራት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸው፣ በቀጣይም የህብረተሰቡን የመኖሪያ ቤት ችግር ለማቃለል አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የአምቦ ከተማ መሬት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መርጋ ወዳጆ በበኩላቸው፤ በወጣው ዕጣ መሰረት ለማህበራቱ የቦታ ርክክብ መደረጉን ገልጸዋል። ዛሬ የቤት መስሪያ ቦታ የተሰጠው በ75 የቤት ማህበራት ለተደራጁ 1 ሺህ 516 ነዋሪዎች ሲሆን ነዋሪዎቹም በተለያዩ ማህበራት ተደራጅተው ከሦስት እስከ ሰባት ዓመት ሲጠባበቁ የቆዩ መሆናቸውን ተናግረዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ ቦታው የተዘጋጀው በአምቦ ከተማ አዋሮ ቆራ ቀበሌ ሲሆን በእዚህም ለእያንዳንዱ ተጠቃሚ 140 ካሬ ሜትር ቦታ ተሰጥቷል። ከዕድሉ ተጠቃሚዎች መካከል መምህራን፣ የመከላከያ ሠራዊት አባላት፣ የጤና ባለሙያዎች፣ የጸጥታና የህግ ባለሙያዎች ይገኙበታል ተብሏል። የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ከተሰጣቸው መካከል ቆንጅት ዱጉማ በሰጡት አስተያየት፤ በተለያዩ ጊዜያት የተሰጣቸውን ግዳጅ እንደተወጡና ለሀገር ላበረከቱት ውለታም የቤት መስሪያ ቦታ በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። የቦታ አሰጣጡ ተግባር ፍትሃዊና ግልጽ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ ጌቱ አዱኛ የተባሉ የጤና ባለሙያ ናቸው። በማህበር ተደራጅተው ለዓመታት ገንዘብ እንደቆጠቡና ከመንግስት ምላሽ ሲጠባበቁ እንደነበር አስታውሰው፣ ከተማ አስተዳደሩ ለጥያቄያቸው ምላሽ በመስጠቱ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። አስተዳደሩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ከማህበራቸው አባላት ጋር በመተባበር የቤት ግንባታውን ለመጀመር እየተዘጋጁ መሆኑንም ገልጸዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በሀገር አቀፍ ደረጃ 30 ሚሊዮን የገጠር መሬት ማሳዎች በዲጂታል የመረጃ ሥርዓት ተመዝግበዋል
Mar 3, 2026 65
ቦንጋ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፡- በሀገር አቀፍ ደረጃ 30 ሚሊዮን የገጠር መሬት ማሳዎች በዲጂታል የመረጃ ሥርዓት መመዝገባቸውን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። የግብርና አገልግሎቶችን ከዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ተግባር እየተከናወነ ነው የግብርና ሚኒስቴር ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጋር በመተባበር ''ዲጂታል ማንነት ለተረጋገጠ ይዞታ ባለቤትነትና ለላቀ የፋይናንስ ተጠቃሚነት'' በሚል መሪ ሀሳብ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። በግብርና ሚኒስቴር የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም መሪ ሥራ አስፈፃሚ ትዕግስቱ ገብረ-መሥቀል እንደገለጹት፣ ሀገራዊ የገጠር መሬት አስተዳደር ሥርዓቱን ለማዘመን በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ካሉ 50 ሚሊዮን ማሳዎች ውስጥ እስካሁን ድረስ 30 ሚሊዮን የሚሆኑት በዲጂታል መረጃ ሥርዓት ተመዝግበው አርሶ አደሩ የይዞታ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት እንዲያገኝ ተደርጓል ብለዋል። የመረጃ ማዘመን ስራው በአሁኑ ወቅት በ516 ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ መደረጉንም ነው ያመለከቱት። አርሶ አደሩ መሬቱን በዋስትና በማስያዝ እስካሁን 10 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የብድር አገልግሎት ማግኘት መቻሉንም አብራርተዋል። በተያዝነው በጀት ዓመት 12 ሚሊዮን አርሶ አደሮችን የፋይዳ መታወቂያ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፣ የመረጃ ስርዓቱን ከዲጂታል መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር አካታች የፋይናንስ ስርዓት ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የዲጂታል መታወቂያ ከይዞታ ማረጋገጫ ጋር መገናኘቱ አርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ይበልጥ ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ በክልሉ የታቀደውን ግብ ለማሳካት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሀብታሙ ካፍትን እና የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፣ የዲጂታል አሰራሩ ለዓመታት ሲነሳ የነበረውን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር እንደሚቀርፍ ጠቁመዋል። መረጃን በዘመናዊ መልኩ ማደራጀትና አርሶ አደሩን የፋይዳ መታወቂያ ባለቤት ማድረግ ላይ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። በመድረኩም የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የስራ ሃላፊዎች፣ የኢትዮ ቴሌኮምና የኢትዮ ፖስታ አገልግሎት የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የግብርና አገልግሎቶችን ከዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ተግባር እየተከናወነ ነው
Mar 3, 2026 76
ቦንጋ፣ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የግብርና አገልግሎቶችን የማዘመንና ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር የማስተሳሰር ተግባር እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ። በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በማገዝ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት ይገባል የክልሉ ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር “ዲጂታል ማንነት ለተረጋገጠ ይዞታ ባለቤትነትና ለላቀ የፋይናንስ ተጠቃሚነት!'' በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው የንቅናቄ መድረኩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለፁት፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ የፋይዳ መታወቂያን ማዳረስ አንዱ ነው። በአሁኑ ወቅትም የገጠር ትራንፎርሜሽንን እውን ለማድረግ ፈጣንና ዘመናዊ የግብርና አገልግሎቶችን ለአርሶና አርብቶ አደሩ መስጠት እንዲቻል እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።ለዚህም የፋይዳ መታወቂያን የማዳረስ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የግብርና አገልግሎቶችን በማዘመን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር የአርሶና አርብቶ አደሩን የብድርና የፋይናንስ ተጠቃሚነት ችግር ለመፍታት እንደሚያስችልም ነው የገለጹት። ይህም አርሶና አርብቶ አደሩ ባለው እሴት ላይ ተመርኩዞ የፋይናንስ ተጠቃሚ እንዲሆን እንደሚያግዘው ነው የተናገሩት። የአርሶና አርብቶ አደሩ ዋነኛ ሀብት የሆነውን የመሬት ልኬትን ከሀገራዊ መረጃ ስርዓት ጋር በማቆራኘትና ከዲጂታል መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር የፋይናንስ ተደራሽነትን የማረጋገጥ ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል። በክልሉ በከተማና በገጠር ከ682 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ መቻሉንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ ናቸው - ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር)
Feb 28, 2026 121
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እና የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ጠንካራ ፍላጎት እንዳላቸው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ በአዘርባጃን ያደረገውን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው የአዘርባጃን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አካዳሚን መጎብኘቱን ገልጸዋል። አካዳሚው በአንድ ዓመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ የትምህርቱ ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሰው ሰራሽ አስተውሎት ተደራሽነት በማስፋት ረገድ ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ከጉብኝቱ መረዳት መቻሉን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከስድስት ዓመታት በፊት መቋቋሙንና ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በጉብኝቱ ወቅት በምርምር እና ዳታ ልውውጥ ላይ በትብብር ለመስራት በሀገራቱ መካከል መግባባት ላይ መደረሱን ነው የተናገሩት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው የአዘርባጃን የሕዝብ አገልግሎት እና ማኅበራዊ ፈጠራ የመንግሥት ኤጀንሲ(ASAN) የፈጠራ ማዕከልን ጎብኝቷል። አሳን የሚሰጠው አገልግሎት ከአንድ መሶብ አገልግሎት ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ በተለይም አገልግሎት አሰጣጡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ መሆኑ ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ያለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሰው ሰራሽ አስተውሎት እንዲታገዝና ጥራቱ እንዲያድግ በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በውይይታቸው በሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ጠቁመዋል። ሀገራቱ በዘርፉ ልምድ ለመለዋወጥ ፍላጎት እንዳላቸውም ነው የተናገሩት። አጠቃላይ ጉብኝቱ ኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ትግበራ ለገባው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና ለዘርፉ ስራዎች አጋዥ አቅም እንደሚሆን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በማገዝ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት ይገባል
Feb 28, 2026 151
ዲመካ፤ የካቲት 21/2018(ኢዜአ)፡- በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በማገዝ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አገኘሁ ተሻገር፤ በደቡብ ኦሞ ዞን ዲመካ ከተማ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለሚገነባው የአርብቶ እና ከፊል አርብቶ አደር የምርምር ኢንስቲትዩት የመሰረተ ድንጋይ አኑረዋል። ዩኒቨርሲቲው የማዕከሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ የምርምር ስራውን መጀመር ይጠበቅበታል ያሉት አፈ ጉባኤው ሀገር በቀል ዕውቀቶችን በመጠቀም በየአካባቢው ያሉ እምቅ ሀብቶችን በሳይንሳዊ ምርምር በማስደገፍ የላቀ ጥቅም እንዲሰጡ ማድረግ ይገባል ብለዋል። የምርምር ማዕከሉ የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች ብቻ የሚጠቀሙበት ሳይሆን በሀገር ውስጥ እና በተለያዩ የዓለም ሀገራት የሚገኙ ተመራማሪዎች የሚሳተፉበትና ልምድ የሚለዋወጡበት እንደሚሆን ገልጸዋል። የምርምር ማዕከሉ በተያዘለት ጊዜ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለሚፈለገው ዓላማ እንዲውል አስፈላጊው እገዛ ድጋፍና ክትትል የሚደረግ ይሆናል ብለዋል። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዮሐንስ ይትባረክ (ዶ/ር)፤ የሚገነባው የምርምር ማእከል በዋነኝነት አራት መሰረታዊ ተልዕኮዎችን ለመፈፀም የሚያስችል ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል። በአካባቢው የግብርና ሥራ እና የእንስሳት ሀብት በሳይንሳዊ የጥናትና ምርምር በማሳደግ የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ አንዱ ሲሆን የቱሪዝም ሀብትን በምርምር በማገዝ ዓለም አቀፋዊ እውቅና እንዲያገኝ ማድረግም ሌላው መሆኑን አንስተዋል። በአካባቢው ያሉ ሀገር በቀል ዕውቀቶችን የመሰነድ፣ የማስተዋወቅ እና የማሳደግ ተልእኮን ለማሳካትም ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት።
ስፖርት
በስፔን ጥሎ ማለፍ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ሪያል ሶሲዬዳድ ከአትሌቲኮ ቢልባኦ የመልስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ
Mar 4, 2026 66
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ሪያል ሶሲዬዳድ ከአትሌቲኮ ቢልባኦ በስፔን ጥሎ ማለፍ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታቸውን ዛሬ ያከናውናሉ። በፕሪሚየር ሊጉ አርሰናል ከብራይተን ማንችስተር ሲቲ ከኖቲንግሃም ፎረስት የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ ጨዋታው ምሽት አምስት ሰዓት ላይ በአኖኤታ ስታዲየም ይካሄዳል። ሁለቱ ቡድኖች የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ በቤናት ቱሪንቴስ ግብ ሪያል ሶሲዬዳድ 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ሪያል ሶሲዬዳድ ከሜዳው ውጪ ባስመዘገበው ድል በአንጻራዊነት ለፍጻሜ የማለፍ እድል በእጁ ይዟል። የባስኩ ክለብ ሪያል ሶሲዬዳድ ሁለት ጊዜ የስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫን አንስቷል። ለመጨረሻ ጊዜ ውድድሩን ያሸነፈው እ.አ.አ በ2019/20 የውድድር ዓመት ነው። ሌላኛው የባስክ ክለብ አትሌቲኮ ቢልባኦ 24 ጊዜ የስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫን በማሸነፍ ከባርሴሎና በመቀጠል ስኬታማው ክለብ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ። ቢልባኦ ለመጨረሻ ጊዜ ውድድሩን ያሸነፈው እ.አ.አ በ2023/24 የውድድር ዓመት ነበር። በደርሶ መልስ የሚያሸንፈው ቡድን በፍጻሜው ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ይገናኛል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ መርሐ-ግብር አትሌቲኮ ማድሪድ ባርሴሎናን በድምር ውጤት 4 ለ 3 በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፏል።
በፕሪሚየር ሊጉ አርሰናል ከብራይተን ማንችስተር ሲቲ ከኖቲንግሃም ፎረስት የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Mar 4, 2026 78
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ29ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ አምስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ብራይተን ከአርሰናል በአሜክስ ስታዲየም ይጫወታሉ። ብራይተን በ37 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። አርሰናል በ64 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ጨዋታው ብራይተን ሶስተኛ ተከታታይ የሊግ ድሉን ለማስመዝገብ የሚያደርገው ነው። ተጋጣሚው አርሰናል ካሸነፈ የሊጉን መሪነት የሚያጠናክርበት ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያገኛል። የ40 ዓመቱ ክሪስ ካቫናግ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ማንችስተር ሲቲ ኖቲንግሃም ፎረስትን ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ላይ በኢትሃድ ስታዲየም ያስተናግዳል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ማንችስተር ሲቲ በ59 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ኖቲንግሃም ፎረስት በ27 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል። ማንችስተር ሲቲ ማሸነፍ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ እንዲቀጥል ያደርገዋል። ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች ያላሸነፈው ኖቲንግሃም ፎረስት ማሸነፍ ላለመውረድ በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያስገኝለታል። የ40 ዓመቱ ዳረን ኢንግላንድ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። ምሽት 5 ሰዓት ከ15 ላይ ኒውካስትል ዩናይትድ ከማንችስተር ዩናይትድ ይጫወታል። ኒውካስትል ዩናይትድ በ36 ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ማንችስተር ዩናይትድ በ51 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ኒውካስትል ከሁለት ተከታታይ ሽንፈቶች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። በማይክል ካሪክ ስር ድንቅ ግስጋሴ እያደረገ የሚገኘው ማንችስተር ዩናይትድ በመልካም ጉዞው ለመቀጠል እና የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ፉክክሩን ለማጠናከር ሶስት ነጥብ ማግኘት ወሳኝ ነው። በቪላ ፓርክ ስታዲየም አስቶንቪላ ከቼልሲ ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ላይ ይጫወታሉ። አስቶንቪላ በ51 ነጥብ አራተኛ፣ ቼልሲ በ45 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዘዋል። በሻምፒዮንስ ሊግ ለመሳተፍ የሚፎካካሩት ሁለቱ ቡድኖች ጠንካራ ፍልሚያ ያደጋሉ። ፉልሃም ከዌስትሃም ዩናይትድ ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ላይ በክራቨን ኮቴጅ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከፋሲል ከነማ ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Mar 4, 2026 59
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 22ኛ ሳምንት ዛሬም ቀጥሎ ሲውል አራት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ሲዳማ ቡና ከፋሲል ከነማ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ የተመልካቾችን ትኩረት ስቧል። ሲዳማ ቡና በሊጉ ካደረጋቸው 21 ጨዋታዎች መካከል 10ሩን ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በዘጠኝ ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በ21ዱ ጨዋታዎች ላይ 26 ጎሎችን ሲያስቆጥር 11 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ39 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው ፋሲል ከነማ በሊጉ 21 ጨዋታዎችን አድርጎ በስምንቱ አሸንፎ በአራቱ ተሸንፎ በቀሪ ስምንት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 16 ግቦችን ሲያስቆጥር 13 ጎሎችን አስተናግዷል። ፋሲል ከነማ በ33 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ሲዳማ ቡና ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ እና የሊጉን መሪነት ለማጠናከር ይጫወታል። ፋሲል ከነማ ካሸነፈ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል ይመለሳል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ወላይታ ድቻ ከሃዋሳ ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ወላይታ ድቻ እስከ አሁን በሊጉ 21 ጨዋታዎችን አድርጎ አራት ጊዜ ሲያሸንፍ ሰባት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ 10 ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 22 ግቦችን ሲያስቆጥር 24 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ22 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ በበኩሉ በሊጉ ባከናወናቸው 21 ጨዋታዎች በ10ሩ ሲያሸንፍ በአምስቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በስድስር ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 24 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 13 ግቦች ተቆጥረውበታል። የሁለት ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ሃዋሳ ከተማ በ36 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ወላይታ ድቻ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ እና ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት ይጫወታል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ ድል ከቀናው ከሁለት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ይመለሳል። ሁለቱ ጨዋታዎች በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከባህር ዳር ከተማ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ኢትዮጵያ ቡና በ26 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ባህርዳር ከተማ በ27 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ኢትዮጵያ ቡና ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ ባህርዳር ከተማ በ21ኛ ሳምንት በአርባምንጭ ከተማ ካስተናገደው ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። አርባምንጭ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። በሊጉ ሁለት ድሎችን ብቻ ያስመዘገበው አርባምንጭ ከተማ በ16 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ28 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ጨዋታው አርባምንጭ ከተማ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው።
ዎልቭስ ሊቨርፑልን አሸነፈ
Mar 4, 2026 80
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 29ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ዎልቭስ ሊቨርፑልን 2 ለ 1 አሸንፏል። በሞለኒው ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሮድሪጎ ጎሜዝ በ78ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ዎልቭስን መሪ አድርጋለች። መሐመድ ሳላህ በ83ኛው ደቂቃ የሊቨርፑልን የአቻነት ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ጨዋታው በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ ሲባል አንድሬ በ94ኛው ደቂቃ ለዎልቭስ የአሸናፊነቱን ጎል አስቆጥሯል። በውድድር ዓመቱ ሶስተኛ ድሉን ያስመዘገበው ዎልቭስ በ16 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። በውድድር ዓመቱ ዘጠነኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሊቨርፑል በ48 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። የወቅቱ የሊጉ የዋንጫ ባለቤት ለሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ ጥሏል። በሌሎች የ29ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ኤቨርተን በርንሌይን 2 ለ 0፣ ሰንደርላንድ ሊድስ ዩናይትድን 1 ለ 0 አሸንፈዋል። ቦርንማውዝ እና ብሬንትፎርድ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
አካባቢ ጥበቃ
የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል
Mar 3, 2026 115
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት እንደሚጠበቅባቸው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ገለጸ። "በምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የሚቋቋም ግብርናን ማስፋፋት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ቀጣናዊ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በኢጋድ፣ የዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ፣ የሥርዓተ ምግብ ፕሮግራም ለምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ፣ የደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምርና ልማት ማስተባበሪያ ትብብር በተዘጋጀው መድረክም የግብርና ማሻሻያ ምክረ ሀሳቦችን እንደሚያፈልቅ ይጠበቃል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ተወካይ ዳህር ኤልሚ፤ በአየር ንብረትና በሥነ-ምኅዳር ደኅንነት የሚከሰት ለውጥ የግብርና ምርታማነት ላይ ጫና እያሳደረ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለው የአፈር መራቆት፣ ድርቅ፣ ጎርፍ፣ ዝናብ እጥረትና በርሃማነት የምስራቅ አፍሪካ የግብርና ምርታማነትና የምግብ ፍጆታ ላይ አሉታዊ ጫና እንደሚያሳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የቀጣናው ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት ለመገንባት የቴክኖሎጂ፣ የግብዓትና የመረጃ ትንተና አቅም መገንባት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣንም የቀጣናውን ሀገራት የግብርና ምርታማነት የሚያሻሽል የአየር ሁኔታ የመረጃ ትንተና ተደራሽ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢኒስቲትዩት የተፈጥሮ ሃብትና የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም ፕሮግራም ዳይሬክተር አወቀ ሙሉዓለም በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ሥርዓት ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችም የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ የአርሶና አርብቶ አደሩን የግብርና ምርታማነት እያሳደገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን፤ የግብርና ምርታማነት የሚያዘምኑ የፋይናንስና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በማስፋት የቀጣናው ሀገራት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር የኢጋድና የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦዌን በበኩላቸው፤ የግብርና ምርታማነትን ማረጋገጥ ለአፍሪካ ዕድገትና ብልጽግና ወሳኝ ነው ብለዋል። የቀጣናውንና አፍሪካን የግብርና ሥርዓት ለማዘመን በሚደረገው ጥረትም የኒውዝላንድ መንግስትና የልማት አጋሮች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች፣ ፖለሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮችና ተመራማሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ስርጭትና መጠን ይጠናከራል
Mar 3, 2026 68
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦በቀጣዮቹ አስር ቀናት በሀገሪቱ የበልግ ሰብል አብቃይ አካባቢዎች የዝናብ መጠንና ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋና እየተጠናከረ እንደሚሄድ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ አራተኛውን የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ሊያስጀምር ነው በኢንስቲትዩቱ የሚቲዎሮሎጂ ትንበያ፣ምክር አገልግሎት እና ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አሳምነው ተሾመ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ለዝናብ መፈጠር ምቹ የሆኑ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ይበልጥ እየተጠናከሩ መሆናቸውን የትንበያ መረጃዎች ያመላክታሉ። የዝናብ ስርጭቱ የሚሸፍናቸው ደቡብና ደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ (ዋነኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑ አካባቢዎች)፣ የስምጥ ሸለቆና አጎራባች አካባቢዎች፣ የመካከለኛውና የደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ምስራቅና ሰሜን ምስራቅ አካባቢዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። በእነዚህ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ የሚጠበቅ ሲሆን፣ በአብዛኛው ስፍራዎች የዝናብ መጠኑ መደበኛና ከመደበኛ በላይ እንደሚሆን ገልጸው፤አልፎ አልፎም ከባድ ዝናብ ሊኖር እንደሚችል ተናግረዋል። የዝናቡ መሻሻል በተለይም ለበልግ አብቃይ አርሶ አደሮች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። በበልግ እየጣለ ያለው ዝናብ የማሳ ዝግጅትና ዘር፡ የአፈር እርጥበትን በማሻሻል አርሶ አደሩ የተለያዩ ሰብሎችን መዝራት እንዲችል ምቹ ሁኔታን በመፍጠር አዎንታዊ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። ለቋሚ ተክሎች፡ ቀደም ብለው ለተዘሩ የበልግ ሰብሎችና በአካባቢው ለሚገኙ ቋሚ ተክሎች ዕድገት ያለውን አስተዋጽኦም ገልጸዋል። ለውሃ አጠር አካባቢዎችም አርሶ አደሩና አርብቶ አደሩ የሚጥለውን የዝናብ ውሃ በማሰባሰብና በማከማቸት ለቀጣይ እንዲጠቀም ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል። በበልግ የሚጥለው ዝናብ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የገጸ ምድር ውሃ መጠን በተለያዩ ተፋሰሶች ላይ እንደሚጨምርም ገልጸዋል። በዚህም ኦሞ ጊቤ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ የላይኛውና መካከለኛው አዋሽ፣መካከለኛና ታችኛው አባይ፣ ገናሌ ዳዋ እና ዋቤ ሸበሌ ተፋሰሶች የተሻለ እርጥበት እንደሚያገኙ ይጠበቃል ብለዋል። በዚህም የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የውሃ ማጠራቀሚያዎችን በመጠቀም የውሃ መጠናቸው ከፍ እንዲል ያደርጋል ብለዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ የአገሪቱ ክፍሎች አሁንም ከፍተኛ የቀን ሙቀት እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በዚህም በጋምቤላ፣ አፋር፣ ሶማሌ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝና ምዕራብ አማራ አካባቢዎች የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት ከ33 እስከ 37 ነጥብ 2 ዲግሪ ሴልሺየስ ሊደርስ እንደሚችል የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ተብሏል።
ኢንስቲትዩቱ አራተኛውን የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ሊያስጀምር ነው
Mar 3, 2026 71
ዳንቦያ፤ የካቲት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ከንባታ ዞን አራተኛውን ዘመናዊ የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳር የመትከል ተግባርን በማጠናቀቅ ስራ ለማስጀመር የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፈጠነ ተሾመ እንደገለጹት፤ ኢንስቲትዩቱ በክልሉ ከንባታ ዞን ዳንቦያ ወረዳ ዳቶ ዳርሀቦራ ተራራ ላይ ነው ዘመናዊ የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳሩን የተከለው። ራዳሩ በ250 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ ያለን የአየር ሁኔታ መረጃ የመሰብሰብ አቅም ያለው ሲሆን፣ የትንተናና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥራዎችን በተሻለ ጥራት ለመከወን ያስችላል ብለዋል። በ14 ሜትር ከፍታ ላይ የተተከለው ይህ ራዳር የዝናብ መጠንን፣ የንፋስ ፍጥነትን፣ የዳመና እንቅስቃሴንና ዝናብ ያዘለ አውሎ ነፋስን የመሳሰሉ መረጃዎችን ከርቀት በመቃኘት ለዋናው የዳታ ማዕከል መረጃ ያስተላልፋል ብለዋል። ይህ የራዳር ጣቢያ በኢትዮጵያና በፊንላንድ መንግሥታት ድጋፍ 13 ሚሊዮን ዩሮ በሚጠጋ በጀት ወደ ሥራ ከሚገቡ ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ፤ አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ለማዘመንና የተሳለጠ መረጃ ለማቅረብ ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም አብራርተዋል። በፕሮጀክቱ የተጠቀሰውን ጨምሮ አራት የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳሮች፣ 10 የአየር ብክለት መከታተያ ጣቢያዎች፣ 10 የመብረቅ መከታተያና ሌሎች የተቀናጁ የሚቲዎሮሎጂ መሠረተ ልማትን የመገንባት ሥራን ያካተተ ነው ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ በ12 ስልታዊ ቦታዎች ላይ የራዳር ጣቢያዎችን ለመትከል እቅድ መያዙን ጠቁመው፤ አራተኛውን ጣቢያ በማጠናቀቅ የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎቱን የማሳደግ አቅሙን አንደሚያጠናከር አስረድተዋል። ራዳሩ በተተከለበት አካባቢ የኃይል መቆራረጥም ሆነ የመረጃ ልውውጥ እንዳይቋረጥ የፀሐይ ብርሃን ኃይል (ሶላር ኢነርጂ) እየተገጠመ ይገኛል ብለዋል። የፕሮጀክቱን የመጨረሻ ምዕራፍ ለመጎብኘት በስፍራው የተገኙት በፊንላንድ ኤምባሲ የትብብር ዘርፍ ኃላፊ ቶሚ ሳርኪኦጃ መንግሥታቸው የኢትዮጵያን ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በመደገፉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
በምስራቅ ቦረና ዞን የእንስሳት መኖ እጥረት እንዳያጋጥም የመኖ ልማት ስራ ከተፋሰስ ጥበቃ ጋር ተቀናጅቶ እየተከናወነ ነው
Mar 3, 2026 63
ነጌሌቦረና፤የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ቦረና ዞን የእንስሳት መኖ እጥረት እንዳያጋጥም የመኖ ልማት ስራ ከተፋሰስ ጥበቃ ጋር ተቀናጅቶ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ ኩልሌ ሸና እንደገለጹት፤ ዞኑ ቆላማና ዝናብ አጠር በመሆኑ በየጊዜው የሚያጋጥመውን የእንስሳት መኖ እጥረት በዘላቂነት ለመቋቋም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። ለዚህም በዘንድሮው የበጋ ወቅት ሕብረተሰቡን በማሳተፍ 105 ተፋሰሶችን መሠረት ያደረገ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች በሚገኙ ተፋሰሶች ላይ የሚካሄደው የተቀናጀ የልማት ሥራ ከ52 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት የሚያካልል መሆኑን አቶ ኩልሌ ጠቁመዋል። ከዚህ ውስጥ በሰው ሰራሽ ጫና እና ከልክ ያለፈ ግጦሽ የተራቆተ ከ38 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ተከልሎ መልሶ እንዲያገግም እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን በተከናወነው እንቅስቃሴ 24 ሺህ 430 ሄክታር የግጦሽ መሬት ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ተከልሎ እንዲያገግም የተደረገ ሲሆን፣ ይህም መኖን በዘላቂነት ለማግኘት የሚደረገውን ጥረት ያግዛል። ከተፈጥሮ ግጦሽ በተጨማሪም በክረምትና በበጋ መስኖ የታገዘ የመኖ ልማት ለማስፋፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ምክትል ኃላፊው አስታውቀዋል። በዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል የአፈርና የድንጋይ እርከን እንዲሁም የጎርፍ መፋሰሻ ቦይ ግንባታ እየተከናወነ ሲሆን የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ዝግጅትንም ጠቅሰዋል። በነዚህ የልማት ሥራዎች ላይ አርሶና አርብቶ አደሮች፣ የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶች በንቃት ተሳትፈዋል። ከዚህም ባለፈ በበልግና በክረምት የሚተከሉ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን የማዘጋጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል። የሊበን ወረዳ የጎቢቻ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ወርቁ አለባቸው በሰጡት አስተያየት፤ አካባቢያቸው ዝናብ አጠር በመሆኑ በተደጋጋሚ ለሚከሰተው የእንስሳት መኖ እጥረት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት ከደረሰባቸው ጉዳት በመማር አሁን ላይ በአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላኛው የቀበሌው ነዋሪ አቶ አልዬ ኢብራሂም በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ እና የእንስሳት መኖ ልማት ለአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው፤ ድርቅንና የአካባቢ መራቆትን ለመቋቋም በአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ላይ ቅድሚያ በመስጠት እንደሚሳተፉ አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቀጣናዊ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Mar 1, 2026 114
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ እያሳደረ ባለው ከፍተኛ ተጽእኖ ምክንያት የቀጣናው የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እና የዜጎች የኑሮ መሰረት አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብ ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል።
የኢጋድ እና ተመድ ትብብር ለቀጣናዊ ሰላም
Feb 26, 2026 155
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት ያላቸውን የጋራ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የኢጋድ የደቡብ ሱዳን ልዩ ልዑክ አምባሳደር ሙሳ ጃማ አሊ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ጉዋንግ ኮንግ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። ልዩ ልዑኮቹ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት በተለይም በደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቅርቡ የአፍሪካ ህብረት የአምስት አባል ሀገራት ኮሚቴ (AU C5) እና ኢጋድ ያደረጉት የጋራ ጉባኤ የተገኙ ውጤቶች ላይም መክረዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ሰላም፣ መረጋጋት እና ቀጣናዊ ትብብር እውን እንዲሆን ያላቸውን ቅንጅት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ሩሲያ በትብብር መሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ
Feb 24, 2026 241
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ሩሲያ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ አጋርነት ዳይሬክተር ታትያና ዶቭጋሌንኮ ጋር በተቋሙ መቀመጫ ጅቡቲ ተወያይተዋል። በውይይቱ ወቅት ኢጋድ እና ሩሲያ በፖሊሲና ደኅንነት፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን፣ ሳይንስ እና ትምህርት ዘርፎች ትብብር ማጎልበት የሚያስችላቸውን ስምምነት እና የድርጊት መርሐ-ግብር ተፈራርመዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ ጉዳዮች ተቀራርበው ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ አጋርነታቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Feb 23, 2026 176
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ በሰላም፣ ልማት እና ዲፕሎማሲ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ(ኢ/ር) ከተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ አፍሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ ለረጅም ጊዜ የቆየ እና ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸው ትብብሩ በጥልቅ የባህል፣ የኢኮኖሚና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ላይ የተመሰረተ መሆኑን አውስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ በአፍሪካ ያላትን ዘላቂ ትብብር እና በአህጉሪቱ እያደገ የመጣውን ኢንቨስትመንት አልፎም በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ያላትን ገንቢ ሚና አድንቀዋል። ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመቀናጀት በሊቢያ፣ ሱዳን እና ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች እያሳየች ያለውን የዲፕሎማሲ ድጋፍ እና ተሳትፎ አዎንታዊ መሆኑን አመልክተዋል። የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ በበኩላቸው የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ በልማት፣ በሰላም እና በባለብዙ ወገን ትብብር ያለውን የመሪነት ሚና አንስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ልማት፣ ሰላም፣ ደህንነት እና ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላትን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች የአፍሪካ ህብረትና ሳዑዲ አረቢያ ያላቸውን ግንኙነት በጋራ መከባበር መንፈስ፣ በወዳጅነት እና በስትራቴጂካዊ አጋርነት ላይ በመመስረት የበለጠ ለማጠናከር የጋራ ፍላጎት ማሳየታቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 146
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 221
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 234
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 678
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 245
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 354
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1097
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1069
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3567
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2378
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8178
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6660
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 332
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 329
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።