ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው - አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ
Mar 21, 2026 76
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሌሎች ሀገራት ትልቅ መነሳሳትን የሚፈጥርና ምሳሌ የሚሆን ፕሮጀክት ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከማጠናከር ባለፈ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው። ይህ መርሃ ግብር በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነ ግዙፍ የደን ልማትና የተፈጥሮ ጥበቃ ዘመቻ ሲሆን የካርቦን ልቀትን በመቀነስ ረገድም በምሳሌነት ተጠቃሽ ነው። ሀገሪቱ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የተፈጥሮ ሥርዓት እንድትገነባ እያገዘም ይገኛል።   በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ ለኢዜአ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የአረንጓዴ አሻራ ፖሊሲ እጅግ የሚደነቅ ጥረት ነው ብለዋል። አረንጓዴ አሻራ ለሌሎች ሀገራትና መሪዎች አርአያ የሚሆን ተሞክሮ እንደሚሆን ጠቁመው ይህ ተግባር ሁላችንም በጋራ እንድንሰራ ያበረታታናል ነው ያሉት። የሀገራት መሪዎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት እየመጡ ያሉ ተግዳሮቶችን ለዜጎች በግልጽ ማሳወቅ እንዳለባቸውና ይህም ዜጎች ለመፍትሄው እንዲሰሩ ያደርጋል ሲሉ ገልጸዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2027 የሚካሄደውን 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመረጧን አምባሳደሩ አድንቀዋል። ኮሎምቢያ እ.ኤ.አ. በ2024 የኮፕ 16 ጉባኤን ማስተናገዷን አውስተው ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን በምታዘጋጅበት ወቅት ሀገራቸው ያካበተችውን ልምድ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። አምባሳደሩ አክለውም የኮሎምቢያን ተሞክሮና የኢትዮጵያን የወደፊት ራዕይ በማጣመር፣ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት ይሰራሉ ብለዋል።
በ3000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ አትሌት ባለሽኝ ባወቀ እና አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ አራተኛና ስድስተኛ ወጥተዋል 
Mar 21, 2026 90
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ21ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ማምሻውን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉባቸው የፍጻሜ ውድድሮች ተደርገዋል።   በ3000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ አትሌት ባለሽኝ ባወቀ 9 ደቂቃ ከ00 ሴኮንድ ከ26 ማይክሮ ሴኮንድ አራተኛ ወጥታለች። በውድድሩ ላይ የተሳተፈችው ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ አትሌት አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ 9 ደቂቃ ከ02 ሴኮንድ ከ41 ማይክሮ ሴኮንድ ስድስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ጣልያናዊቷ አትሌት ናዲያ ባቶክሌቲ 8 ደቂቃ ከ57 ሴኮንድ ከ64 ማይክሮ ሴኮንድ አንደኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች። አሜሪካዊቷ ኤሚሊ ማክካይ ሁለተኛ እና አውስትራሊያዊቷ ጄሲካ ሁል ሶስተኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን አጠናቀዋል።   በወንዶች የ3000 ሜትር የፍጻሜ ውድድር አትሌት አዲሱ ይሁኔ 7 ደቂቃ ከ38 ሴኮንድ ከ60 ማይክሮ ሴኮንድ ስምንተኛ ወጥቷል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ጌትነት ዋለ 7 ደቂቃ ከ40 ሴኮንድ ከ21 ማይክሮ ሴኮንድ 12ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። የታላቋ ብሪታኒያ አትሌት ጆሽ ኬር 7 ደቂቃ ከ35 ሴኮንድ ከ56 ማይክሮ ሴኮንድ አንደኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳሊያ አግኝቷል። አሜሪካዊው ኮል ሆከር ሁለተኛ ሲወጣ ፈረንሳዊው ያን ሽሩብ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። በፖላንድ ቶሩን ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። ሻምፒዮናው ነገ ይጠናቀቃል።
የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት ሰጥቷል
Mar 21, 2026 91
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሚያስችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ራቢ (ኢ/ር) ገለጹ። የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ እና ጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ኢንቨስትመንትስ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።   ስምምነቱ በኢትዮጵያ በኢነርጂ ዘርፍ የክህሎት ልማትን፣ ኢኖቬሽን እና ዘላቂ የኢነርጂ ልማትን ለማሳደግ ያለመ እንደሆነ ተመላክቷል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ስምምነቱ ለዩኒቨርሲቲው ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ አለው። በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የንድፈ ሐሳብ ትምህርትን ከኢንዱስትሪው የተግባር ልምድ ጋር በማቀናጀት ለሀገር ግንባታ የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ የሚያካሂዳቸው ጥናትና ምርምሮች ለጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ፕሮጀክቶች ግብዓት ከመሆናቸው ባሻገር ከኩባንያው የሚገኘው ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ዕውቀት ለተማሪዎችና ለሀገር የኢነርጂ ዘርፍ ትልቅ አቅም ይፈጥራልም ነው ያሉት። ዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሚያስችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት መስጠቱን እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል።   የጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ኢንቨስትመንትስ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ፕሬዚዳንት ሱን ዦንግ እንዳሉት፤ ስምምነቱ በቻይና እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የኢንዱስትሪ እና የትምህርት ትስስር ለማሳደግ የሚያስችል ነው። በአካዳሚክ እና በኢንዱስትሪ መካከል የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ለመፍጠር ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነም አስረድተዋል። ጂ.ሲ.ኤል በኢነርጂ፣ ኢንጂነሪንግ፣ በቴክኒክ፣ በትምህርት፣ በምርምርና ፈጠራ ዘርፍ ጠንካራ አቅም እንዲሁም ውጤታማ የሰው ኃይል ለማፍራት እንደ ቁልፍ ማዕከል እንደሚያገለግል አስገንዝበዋል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 21, 2026 171
ከመጋቢት 6 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ማሳሰቢያ በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ስለዚህ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በኃላፊነት ልንጠቀም ይገባል ሲሉ ያሳሰቡት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ባሳለፍነው ሳምንት … ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል ፕሬዚዳንት ታዬ ያስጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባሳለፍነው ሳምንት የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑን ገልጸው፤ የሕይወት ምሉዕነት የሚረጋገጠው ካለው ላይ ቆርሶ በመስጠት መሆኑን አስገንዝበዋል። ለተቸገሩ መድረስና ለወገን መቆም ትልቅ የመንፈስ ዕርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ መጠናከር እንዳለበትም አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ የተወያዩት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጉብኝት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በእንዶዴ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ እና በኤ ኤም ጂ (AMG) - እንዶዴ የባቡር መሥመር ፕሮጀክቶች ላይ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። እነዚህ በራስ ዐቅም የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነታችንን ከማሻሻል ባለፈ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ያጸናሉ ሲሉም በዚሁ ወቅት በአጽንዖት ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ጋር በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ መሥተዳድሮች፣ ከከተማ አሥተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ሥርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ሥርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1 ሺህ 452 ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሐሴ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ረመዳን ወር ተጠናቅቆ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት የተከበረው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ለበዓሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች የፌደራል፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። #ባሳለፍነው_ሣምንት #ኢዜአ
የሚታይ
መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ለአገር አንድነትና ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሰጥተው መስራት ይጠበቅባቸዋል
Mar 21, 2026 208
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ለአገር አንድነትና ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የልኅቀት ማዕከል የልዩ ትኩረት ዘርፍ ጋዜጠኝነት የመጀመሪያው ዙር ሠልጣኞች የማጠናቀቂያ መርሃ-ግብር ተካሂዷል። አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ለማንኛውም ዘገባ ብሔራዊ ጥቅምን ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባ አሳስበዋል። ባለሙያዎች የሕዝብና የአገርን ጥቅም በዘላቂነት የሚያረጋግጡ ሥራዎች ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ውስጣዊ አንድነትን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅመው፤ ለጠንካራ አገር እውን መሆን በአንድ ዓላማ መቆም ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። በዚህ ረገድ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች አሰባሳቢ ሚናቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባም አመልክተዋል። ባለሙያዎች ግጭትን ከሚያባብሱ ዘገባዎች ራሳቸውን ማራቅ እንዳለባቸው አሳስበው፤ ሙያዊ መርሆዎችን ተከትሎ መዘገብና መሥራት ከባለሙያዎች የሚጠበቅ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የሕግ የበላይነት እንዲከበር፣ በሠላምና መረጋጋት ዙሪያም ባለሙያዎች ቅድሚያ የሚሰጡት አጀንዳ መሆን እንዳለበት ጠቅሰው፤ እነዚህን ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመተግበር የሚያስችል በቂ አቅም ሊኖራቸው እንደሚገባም አስታውቀዋል። ጋዜጠኞች የሚጠበቅባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ የሚደረገው ድጋፍም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በልማት ረገድም የኢትዮጵያ ግቦች እንዲሳኩ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ትልቅ ድርሻ እንዳላቸውም ጠቅሰው፤ ሙስናን በተግባር ሊታገሉ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
በመሬት ናዳ የተፈናቀሉ ወገኖችን ለማቋቋም የባለድርሻ አካላት ሚና እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ
Mar 21, 2026 110
አርባምንጭ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በጋሞ ዞን በመሬት ናዳ አደጋ የተፈናቀሉ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ሚና እንዲጠናከር የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ።   ኮሚሽንኑ በጋሞ ዞን በመሬት ናዳ አደጋ የተፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም በሚያስችሉ ሳይንሳዊ ጥናቶች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል። የኮሚሽንኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ በመሬት ናዳ አደጋ የተፈናቀሉትንና በአደጋ ስጋት ላይ የሚገኙ ሰዎችን መልሶ ለማቋቋም ተቋማቸው ሚናውን እንደሚወጣ ገልጸዋል። የበልግ ዝናቡ እንደሚቀጥል ጠቁመው፤ ተጨማሪ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት እንዳይደርስ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት በትኩረት እንዲሠራ አሳስበዋል።   የተለያዩ አጋሮች የዕለት ደራሽ ድጋፍ ከማድረግ ጎን ለጎን ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረጉ ጥረቶች እየተወጡ ያለውን አስተዋፅዖ እንዲያጠናክሩም ጠይቀዋል። ተፈናቃዮች በሚሰፍሩባቸው አካባቢዎች ትምህርት፣ ጤና፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ አገልግሎትን ጨምሮ የማኅበራዊና የመሠረተ-ልማት ሥራዎችን በማከናወን ከመንግሥት ጎን መቆም እንዳለባቸው አመልክተዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት አመራርና የምግብ ዋስትና ኮሚሽን ኮሚሽነር ወገኔ ብዙነህ በበኩላቸው፤ ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ቦታዎች መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል።
መገናኛ ብዙኃን ለአሰባሳቢ ትርክት ግንባታ የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል
Mar 21, 2026 243
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- መገናኛ ብዙኃን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር ለአሰባሳቢ ትርክት ግንባታ የሚያበረክቱትን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀኔራልና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ።   የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የልኅቀት ማዕከል የልዩ ትኩረት ዘርፍ ጋዜጠኝነት የመጀመሪያው ዙር ሠልጣኞችን እያስመረቀ ነው። በዚሁ ወቅት አምባሳደር ሬድዋን፤ መገናኛ ብዙኃን ሀገር መገንቢያ ቁልፍ መሣሪያዎች መሆናቸውን አስገንዝበዋል። ስለዚህ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር ለአሰባሳቢ ትርክት ግንባታ የሚያበረክቱትን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት። ለዚህ ደግሞ የሀገርን መዳረሻ ርዕይ፣ ግብና ብሔራዊ ጥቅም በቅጡ የተገነዘበ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያ ማፍራት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።   የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የልኅቀት ማዕከል የልዩ ትኩረት ዘርፍ የጋዜጠኝነት ሥልጠናም የባለሙያዎችን ዕውቀትና ክኅሎት በማዳበር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አመላክተዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብሩ የይዘት ሥራዎችን በማመንጨት የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና የሕዝብ አንድነት የመገናኛ ብዙኃን የትኩረት ማዕከል ሊሆን እንደሚገባ ም ነው ያሳሰቡት።
1447ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል በሰላም ተጠናቋል - የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ
Mar 20, 2026 254
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2018(ኢዜአ)፦ በመላው ሀገሪቱ የተከበረው 1,447ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል በሰላም መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል። በዓሉ በስኬት እንዲጠናቀቅ ‎የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ሰፊ የሰው ኃይል በማሰማራት ተገቢውን የፀጥታ ሥራ በማከናወን ኃላፊነቱን በሚገባ መወጣቱንም ገልጿል።   ከበዓሉ ዋዜማ ጀምረው በተለያዩ አካባቢዎች የተጠናከረ ጥበቃ በማከናወን በዓሉ በስኬት እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታቸውን በብቃት ለተወጡ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት አመራሮችና አባላት ላቅ ያለ ምስጋና አቅርቧል። በተመሳሳይ ለፀጥታና ደኅንነት አካላት አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን ድርሻ ላበረከተው ለመላው የሀገራችን ሕዝብ፣ ለሃይማኖት አባቶች፣ ለበዓሉ አስተባባሪዎች፣ ለእምነቱ ተከታዮች እና ለወጣቶች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አመስግኗል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የነጻ የአየር ሰዓት ድልድሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን የሚያስተዋውቁበት መድረክ ነው
Mar 21, 2026 139
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018(ኢዜአ)፦ የነጻ የአየር ሰዓት ድልድሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን በነፃነት ለህዝብ የሚያስተዋውቁበት መድረክ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ንዋይ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንና የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በፖለቲካ ፓርቲዎች የነጻ የአየር ሰዓት ድልደላና አጠቃቀም ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሂደዋል። አቶ ተስፋዬ ንዋይ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የነጻ የአየር ሰዓት ድልድሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ፖሊሲያቸውን ለህዝብ የሚያስተዋውቁበት መድረክ ነው። ቦርዱ ከመገናኛ ብዙኅን ባለስልጣን ጋር መመሪያ በማዘጋጀት የተተገበረው የነጻ አየር ሰዓት ድልድል ለምርጫው ነፃ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሕዊነት መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ድረስ ከ18 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የድምፅ መስጫ ካርድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል። በዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመደበላቸውን የነጻ አየር ሰዓት በመጠቀም የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ ማቅረብ እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ሰለሞን ታፈሰ፤ የነጻ አየር ሰዓት ድልድል ሥርዓቱ በምርጫ ፉክክር ሂደቱ የፖሊሲ አማራጮቻችንን በፍትሕዊነት ለህዝብ ለማቅረብ ጉልህ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ አባል ከማል ሰዒድ፤ የነጻ የአየር ሰዓት ድልድሉን በመጠቀም የፖሊሲ አማራጭ ሃሳቦች ለህዝብ እንደሚቀርቡ ገልጸዋል። የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀ መንበር ነጻነት ጣሰው በበኩላቸው፤ የድልድል ሥርዓቱ ህዝቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የፖሊሲ ሃሳብ በዕውቀት ላይ ተመሰረቶ ድምፅ እንዲሰጥ ያስችላል ብለዋል። የዶንጋ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀ መንበር ዓለሙ ከበደ፤ ድልድሉ በምክክርና ግልጽ መስፈርት መደረጉ የምርጫ ሂደት መተማመንን የሚያጎለብት ወሳኝ አሰራር መሆኑን ተናግረዋል። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ደምሴ ስኳሬ፤ የፖሊሲ አማራጭ መፎካከሪያ የአየር ሰዓት ድልድሉ ዴሞክራሲዊ የምርጫ ባህልን ለማጎልበት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አንሰተዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ግዛው ተስፋዬ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመደበላቸውን የአየር ሰዓትና የጋዜጣ አምድ በአግባቡ መጠቀም እደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። መገናኛ ብዙሃንም የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጫቸውን ለህዝብ የሚቀርቡበትን የአየር ሰዓት ሙያዊ ገለልተኝነትና ሚዛናዊነትን በማስጠበቅ ለሃሳብ የበላይነት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የነጻ የአየር ሰዓት ለሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች 40 በመቶ፣ ባስመዘገቡት ዕጩዎች ብዛት 25 በመቶ፣ የሴት ዕጩዎች 15 በመቶ፣ አካል ጉዳተኞች 15 በመቶ እና ሴት አካል ጉዳተኞች 5 በመቶ ባስመዘገቡት መሠረት የሚደለደል መሆኑን ተገልጿል። Ethiopian News Agency #ኢዜአ #7ኛው_ጠቅላላ_ምርጫ
መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ለአገር አንድነትና ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሰጥተው መስራት ይጠበቅባቸዋል
Mar 21, 2026 208
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ለአገር አንድነትና ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የልኅቀት ማዕከል የልዩ ትኩረት ዘርፍ ጋዜጠኝነት የመጀመሪያው ዙር ሠልጣኞች የማጠናቀቂያ መርሃ-ግብር ተካሂዷል። አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ለማንኛውም ዘገባ ብሔራዊ ጥቅምን ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባ አሳስበዋል። ባለሙያዎች የሕዝብና የአገርን ጥቅም በዘላቂነት የሚያረጋግጡ ሥራዎች ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ውስጣዊ አንድነትን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅመው፤ ለጠንካራ አገር እውን መሆን በአንድ ዓላማ መቆም ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። በዚህ ረገድ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች አሰባሳቢ ሚናቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባም አመልክተዋል። ባለሙያዎች ግጭትን ከሚያባብሱ ዘገባዎች ራሳቸውን ማራቅ እንዳለባቸው አሳስበው፤ ሙያዊ መርሆዎችን ተከትሎ መዘገብና መሥራት ከባለሙያዎች የሚጠበቅ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የሕግ የበላይነት እንዲከበር፣ በሠላምና መረጋጋት ዙሪያም ባለሙያዎች ቅድሚያ የሚሰጡት አጀንዳ መሆን እንዳለበት ጠቅሰው፤ እነዚህን ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመተግበር የሚያስችል በቂ አቅም ሊኖራቸው እንደሚገባም አስታውቀዋል። ጋዜጠኞች የሚጠበቅባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ የሚደረገው ድጋፍም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በልማት ረገድም የኢትዮጵያ ግቦች እንዲሳኩ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ትልቅ ድርሻ እንዳላቸውም ጠቅሰው፤ ሙስናን በተግባር ሊታገሉ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና አሳታፊ እንዲሆን የድርሻዬን እየተወጣሁ ነው -ኦቢኤን
Mar 21, 2026 136
አዳማ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና አሳታፊ እንዲሆን የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኦቢኤን) አስታወቀ። በምርጫ ወቅት መገናኛ ብዙሃን ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና ለምርጫው ስኬታማነት የማይተካ ሚና ያላቸው ሲሆን በተለይም መረጃን ተደራሽ ማድረግና ግንዛቤ መፍጠር፣ የፖለቲካ አማራጮችን ማስተዋወቅና የምርጫ ክርክሮችን ያዘጋጃሉ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ አሳታፊ እና አካታች እንዲሆን መገናኛ ብዙሃን እንደ ባለድርሻ አካል ሚናቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኦቢኤን) ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አንዋር ጀማል ተቋሙ ስርጭት በሚያከናውንባቸው ሁሉም ቋንቋዎች ምርጫውን በተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ሕዝቡ በቂ ግንዛቤ ጨብጦ በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲኖረው ከማድረግ አንጻር ሁሉንም የምርጫ ባለድርሻ አካላት ባሳተፈ መልኩ ጥረት እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይም የፖለቲካ ፓርቲዎች የየራሳቸውን ፖሊሲ፣ ስትራቴጂና አማራጭ ሃሳቦች ለሕዝቡ ማስተዋወቅ እንዲችሉ እድል ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ ተከታታይ የምርጫ ክርክር መድረኮችን በማዘጋጀት የምርጫ ማኑፌስቷቸውን እንዲያስተዋውቁ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። ተፎካካሪ ፓርቲዎች ተቋሙ ለስርጭት በሚጠቀምባቸው ቋንቋዎች አማራጭ ሃሳባቸውን ለሕዝብ ተደራሽ ማድረጋቸው የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋትና የምርጫ አውዱ እንዲጠናከር የጎላ ሚና እንዳለውም አስረድተዋል። ተቋሙ የምርጫ ዴስክ በማደራጀት በጠቅላላ ምርጫው ዙሪያ ሰፋ ያሉ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው ለጋዜጠኞች በምርጫ ሥነ-ምግባር፣ ደንቦችና ሕጎች ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ ወቅትና በድህረ ምርጫ ወቅት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ሊከተሏቸው በሚገቡ የሙያ ሥነ-ምግባርና የዘገባ አዘጋገብ ዘዴዎች ላይ ተከታታይ ሥልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑንም ገልጸዋል። ተቋሙ ከቴሌቪዥን ጣቢያው ባሻገር በኮርፖሬሽኑ ሥር ባሉ የኤፍ.ኤም ሬዲዮዎች በየዞኑ ጠቅላላ ምርጫውን የተመለከቱ ስራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት በምርጫ ሂደት የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ ነው
Mar 21, 2026 174
ዲላ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ):- ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት በምርጫ ሂደት የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ። "በኢትዮጵያ ምርጫ የማካሔድ ፋይዳዎች ለሀገር ግንባታ፣ ለሰላም፣ ለልማት እና ብልፅግና ያለው አንደምታ" በሚል መሪ ሃሳብ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች፣ በርካታ ምሁራን እና የተለያዩ ባለደርሻ አካላት በመድረኩ ተገኝተዋል።   በመድረኩ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ዲን፣ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ዘለቀ አርፍጮ፤ የምርጫ ሂደት ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። የምርጫ ሂደት የዜጎችን የፖለቲካ ተሳትፎና የመወሰን መብት የሚያጎናጽፍ እና ፓርቲዎችም ለሀገርና ህዝብ የሚጠቅሙ ፖሊሲና ስትራቴጂዎች የሚያመነጩበት ስለመሆኑ አስረድተዋል። በመሆኑም ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት በምርጫ ሂደት የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን የፖለቲካ ፓርቲዎች ፉክክርና የህዝቡ ተሳትፎ በጥሩ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን አንስተው ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ገልጸዋል።   የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ ዓለሙ (ዶ/ር)፤ በበኩላቸው በሁሉም ረገድ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማካሄድ የኢትዮጵያን ሀገረ መንግስት ግንባታ ማጽናት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በመሆኑም በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀሳባቸውን እንዲያንሸራሽሩ መድረክ በመፍጠር ዜጎች የጠራ ግንዛቤ ይዘው መምረጥ እንዲችሉ ሚዲያዎች ሃላፊነታቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል።   ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት በዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳቦች እንዲሁም የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ የተለያዩ ሀሳቦችን እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ እየፈጠርን ነው - የሚዲያ ተቋማት
Mar 21, 2026 168
ሐዋሳ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ) :- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሀሳባቸውን ለህዝብ እንዲያቀርቡ መረጃን ተደራሽ በማድረግ ምቹ ሁኔታን እየፈጠሩ መሆናቸውን የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ ለማካሔድ ቀነ ቀጠሮ መያዙ የሚታወቅ ሲሆን ተሳታፊ ፓርቲዎችም የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ። በዚህም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያሏቸውን አማራጮችና የፓርቲ ፕሮግራም ለመራጩ ህዝብ የማስተዋወቅና የክርክር መድረኮችን በማካሔድ ላይ የሚገኙ ሲሆን በሀገሪቱ የሚገኙ የሚዲያ ተቋማትም ይህን ሃላፊነት እየተወጡ ይገኛሉ። ይህም መራጩ ህዝብ የፖለቲካ ፓርቲዎቹን የፖሊሲ አማራጭ ጠንቅቆ በማወቅ ትክክለኛ ውሳኔ እንዲወስን እድልን እንደሚፈጥር እሙን ነው። ኢዜአ የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እና የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሥራ ሃላፊዎችን በምርጫው ዙሪያ ለህዝቡ መረጃዎችን በማድረስ ረገድ ሃላፊነታቸውን ለመወጣት እያከናወኑት ስላለው ተግባር ጠይቋል።   የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ ዘላለም ገነሞ እንዳሉት ድርጅቱ ለምርጫው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የፖለቲካ ፓርቲዎች ይዘው የመጡትን የፖሊሲ አማራጮች እንዲያስተዋውቁ እያደረገ ይገኛል። በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች የሚንቀሳቀሱና በምርጫው የሚሳተፉ ፓርቲዎች በቴሌቪዥን የሚከራከሩበትን መድረክ በማዘጋጀት አመራጮቻቸውን እንዲያስተዋውቁ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ተናግረዋል። የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በዋና ጣቢያውና ባሉት ቅርንጫፎች በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በዲጂታል ሚዲያውና በጋዜጣ በ50 ቋንቋዎች ስለምርጫው ለህዝብ መረጃ እያደረሰ እንደሚገኝ አቶ ዘላለም ገልጸዋል። ድርጅቱ ከምርጫ ቦርድና ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው በቀጣይ ለፓርቲዎቹ በሚሰጠው የአየር ሰዓት ድልድል መሰረት ለማስተናገድ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።   የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈጻሚና የይዘት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አደገ አየለ ሲቢሲ በምርጫው የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚኖራቸው መድረኮች በመገኘት መረጃዎችን ለህዝቡ እያደረሰ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኮርፖሬሽኑ አጀንዳ በመቅረጽ ምርጫን በተመለከተ ከህብረተሰቡ ጋር ውይይቶችን በማድረግ አስተያየቶችን በመሰብሰብ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። ለማህበረሰቡ በሲዳምኛና በአማርኛ ቋንቋዎች ምርጫውን የተመለከቱ መረጃዎች እንዲደርሱት በቴሌቪዥንና በዲጂታል ሚዲያው እያሰራጨ ነው ብለዋል።
የተሻለ ሐሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች
Mar 21, 2026 182
ሠመራ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በዘንድሮው ምርጫ ለመሳተፍ የሚያስችለንን ካርድ በመጠቀም የተሻለ ሐሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ቀኑን እየጠበቅን ነው ሲሉ የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ነዋሪዎች መካከል ሃስና መሐመድ እንዳሉት፤ በዘንድሮው ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች እያካሄዱ ያሉትን የምርጫ ክርክር እየተከታተሉ ነው።   በዚህም የተሻለ ሐሳብ እያንፀባረቀ ያለውን ፓርቲ ለመለየት መቻላቸውን አንስተዋል። ሌሎቹ አስተያየት ሰጭዎች ዘሐራ ኢድሪስና ሃዋ ኢድሪስም፤ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸው ይበጀኛል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። ካርድ ያልወሰዱ ነዋሪዎች ካርድ በማውጣት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙም መክረዋል። በመራጭነት ለመሳተፍ የመጀመሪያው መሆኑን የገለጸው አብዱ ሁሴን በበኩሉ፤ በምርጫው ለመሳተፍ የምርጫ ቀኑ እስከሚደርስ እየጠበቀ መሆኑን ተናግሯል። እየተካሄዱ ያሉ የምርጫ ክርክሮችን እየተከታተለ መሆኑን ጠቁሞ፤ ይህም ሀገሬን ሊመራ የሚችለው ፓርቲ የትኛው ነው የሚለውን እንድለይ አስችሎኛል ብሏል። ምርጫ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የምንፈልገውን ፓርቲ የምንመርጥበት ልዩ ዕድል መሆኑን ተረድቼ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጭ ሐሰን መሐመድ ናቸው።
የምርጫ ካርድ በመያዝ ለኢትዮጵያ የተሻለ የሚሰራውን ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች
Mar 21, 2026 142
ሚዛን አማን፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ለኢትዮጵያ እድገት በንቃት መስራት የሚችለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጁ ሆነናል ሲሉ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተናገሩ። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካታች፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ለማከናወን የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ሂደቶችን እየተገበረች ነው። ምርጫው በአሳታፊነቱ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችንም የሚያካትት በመሆኑ ኢዜአ ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር ቆይታ አድርጎ ተማሪዎቹ በምርጫው ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በትምህርት ላይ ቢሆኑም ያላቸውን ጊዜ በመጠቀም ካርድ ወስደው በሀገር ጉዳይ ላይ በድምጽ የመወሰን ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙበትም አረጋግጠዋል። የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ጌታቸው በላቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ እንደሚሳተፍ ገልጾ ለዚህም የምርጫ ካርድ በመውሰድ የተሻለ ሀሳብ የያዘ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቱን ተናግሯል። በዚህም ካርዱን በመውሰድ የምርጫው ጊዜውን በጉጉት እየጠበቀች መሆኑን የተናገረችው ደግሞ ተማሪ ሰናይት ረዳይ ነች። እንደ ዜጋ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ግዴታችን በመሆኑ በእያንዳንዱ የምርጫ ሂደት ሕጉ በሚፈቅደው መንገድ ተሳትፈን የዴሞክራሲ ልምምድን ማጠናከር አለብን ብላለች። ተማሪ ታምሩ ገብረ ማርያም እና ተማሪ አቤል ሳምሶን በበኩላቸው በካርድ ድምጻችንን ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት ከወዲሁ እያደረግን ነው ብለዋል። ከመምረጥ ባሻገር የምንመርጠውን ፓርቲ ፖሊሲ ለይቶ መረዳትና ለኢትዮጵያ እድገት የተሻለ የሚሰራውን በቅድመ ምርጫ ጊዜ መለየት ይጠበቅብናል የሚል ሀሳብ አጋርተዋል። ሌሎች ተማሪዎችም በትምህርት የሚያውቁትን የምርጫ ሥነ ሥርዓት በተግባር ለማረጋገጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ተመዝግበው መውሰድና ለምርጫው መዘጋጀት እንዳለባቸውም አመልክተዋል።  
ነጻ የዓየር ሠዓት አጠቃቀም ለምርጫ ሂደት ዴሞክራሲያዊነት ወሳኝ ሚና አለው
Mar 21, 2026 134
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የነጻ የዓየር ሠዓት አጠቃቀም ለምርጫ ሂደት ዴሞክራሲያዊነት እና ፍትሐዊነት ወሳኝ ሚና እንዳለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን እና የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በተገኙበት፤ በፖለቲካ ፓርቲዎች ነጻ የዓየር ሠዓት ድልድልና አጠቃቀም ላይ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡   አቶ ተስፋዬ ንዋይ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ነጻ የዓየር ሠዓት ፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውንና ማኑፌስቷቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት ወሳኝ መድረክ ነው። ይህ አሠራር የምርጫ ሂደቱ ዴሞክራሲያዊ፣ ግልጽ እና ፍትሐዊ መሆኑን ከሚያሳዩ መገለጫዎች አንዱ ነው ብለዋል። ቦርዱ ከመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ጋር በመተባበር ነጻ የዓየር ሠዓት አጠቃቀምን የሚመራ መመሪያ አዘጋጅቶ ወደ ሥራ መግባቱንም አስታውቀዋል።   ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኃን የሚሰጣቸውን ነጻ የዓየር ሠዓት እና የጋዜጣ ዐምድ ለምርጫ ቅስቀሳ ሥራቸው በአግባቡ እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል። ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ከ18 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ዜጎች ለመራጭነት መመዝገባቸውንም አመላክተዋል።
ፖለቲካ
የነጻ የአየር ሰዓት ድልድሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን የሚያስተዋውቁበት መድረክ ነው
Mar 21, 2026 139
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018(ኢዜአ)፦ የነጻ የአየር ሰዓት ድልድሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን በነፃነት ለህዝብ የሚያስተዋውቁበት መድረክ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ንዋይ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንና የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በፖለቲካ ፓርቲዎች የነጻ የአየር ሰዓት ድልደላና አጠቃቀም ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሂደዋል። አቶ ተስፋዬ ንዋይ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የነጻ የአየር ሰዓት ድልድሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ፖሊሲያቸውን ለህዝብ የሚያስተዋውቁበት መድረክ ነው። ቦርዱ ከመገናኛ ብዙኅን ባለስልጣን ጋር መመሪያ በማዘጋጀት የተተገበረው የነጻ አየር ሰዓት ድልድል ለምርጫው ነፃ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሕዊነት መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ድረስ ከ18 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የድምፅ መስጫ ካርድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል። በዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመደበላቸውን የነጻ አየር ሰዓት በመጠቀም የፖሊሲ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ ማቅረብ እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ሰለሞን ታፈሰ፤ የነጻ አየር ሰዓት ድልድል ሥርዓቱ በምርጫ ፉክክር ሂደቱ የፖሊሲ አማራጮቻችንን በፍትሕዊነት ለህዝብ ለማቅረብ ጉልህ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ አባል ከማል ሰዒድ፤ የነጻ የአየር ሰዓት ድልድሉን በመጠቀም የፖሊሲ አማራጭ ሃሳቦች ለህዝብ እንደሚቀርቡ ገልጸዋል። የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀ መንበር ነጻነት ጣሰው በበኩላቸው፤ የድልድል ሥርዓቱ ህዝቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የፖሊሲ ሃሳብ በዕውቀት ላይ ተመሰረቶ ድምፅ እንዲሰጥ ያስችላል ብለዋል። የዶንጋ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀ መንበር ዓለሙ ከበደ፤ ድልድሉ በምክክርና ግልጽ መስፈርት መደረጉ የምርጫ ሂደት መተማመንን የሚያጎለብት ወሳኝ አሰራር መሆኑን ተናግረዋል። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ደምሴ ስኳሬ፤ የፖሊሲ አማራጭ መፎካከሪያ የአየር ሰዓት ድልድሉ ዴሞክራሲዊ የምርጫ ባህልን ለማጎልበት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አንሰተዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ግዛው ተስፋዬ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመደበላቸውን የአየር ሰዓትና የጋዜጣ አምድ በአግባቡ መጠቀም እደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። መገናኛ ብዙሃንም የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጫቸውን ለህዝብ የሚቀርቡበትን የአየር ሰዓት ሙያዊ ገለልተኝነትና ሚዛናዊነትን በማስጠበቅ ለሃሳብ የበላይነት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የነጻ የአየር ሰዓት ለሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች 40 በመቶ፣ ባስመዘገቡት ዕጩዎች ብዛት 25 በመቶ፣ የሴት ዕጩዎች 15 በመቶ፣ አካል ጉዳተኞች 15 በመቶ እና ሴት አካል ጉዳተኞች 5 በመቶ ባስመዘገቡት መሠረት የሚደለደል መሆኑን ተገልጿል። Ethiopian News Agency #ኢዜአ #7ኛው_ጠቅላላ_ምርጫ
መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ለአገር አንድነትና ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሰጥተው መስራት ይጠበቅባቸዋል
Mar 21, 2026 208
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ለአገር አንድነትና ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የልኅቀት ማዕከል የልዩ ትኩረት ዘርፍ ጋዜጠኝነት የመጀመሪያው ዙር ሠልጣኞች የማጠናቀቂያ መርሃ-ግብር ተካሂዷል። አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ለማንኛውም ዘገባ ብሔራዊ ጥቅምን ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባ አሳስበዋል። ባለሙያዎች የሕዝብና የአገርን ጥቅም በዘላቂነት የሚያረጋግጡ ሥራዎች ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ውስጣዊ አንድነትን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅመው፤ ለጠንካራ አገር እውን መሆን በአንድ ዓላማ መቆም ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። በዚህ ረገድ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች አሰባሳቢ ሚናቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባም አመልክተዋል። ባለሙያዎች ግጭትን ከሚያባብሱ ዘገባዎች ራሳቸውን ማራቅ እንዳለባቸው አሳስበው፤ ሙያዊ መርሆዎችን ተከትሎ መዘገብና መሥራት ከባለሙያዎች የሚጠበቅ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የሕግ የበላይነት እንዲከበር፣ በሠላምና መረጋጋት ዙሪያም ባለሙያዎች ቅድሚያ የሚሰጡት አጀንዳ መሆን እንዳለበት ጠቅሰው፤ እነዚህን ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመተግበር የሚያስችል በቂ አቅም ሊኖራቸው እንደሚገባም አስታውቀዋል። ጋዜጠኞች የሚጠበቅባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ የሚደረገው ድጋፍም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በልማት ረገድም የኢትዮጵያ ግቦች እንዲሳኩ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ትልቅ ድርሻ እንዳላቸውም ጠቅሰው፤ ሙስናን በተግባር ሊታገሉ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና አሳታፊ እንዲሆን የድርሻዬን እየተወጣሁ ነው -ኦቢኤን
Mar 21, 2026 136
አዳማ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና አሳታፊ እንዲሆን የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኦቢኤን) አስታወቀ። በምርጫ ወቅት መገናኛ ብዙሃን ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና ለምርጫው ስኬታማነት የማይተካ ሚና ያላቸው ሲሆን በተለይም መረጃን ተደራሽ ማድረግና ግንዛቤ መፍጠር፣ የፖለቲካ አማራጮችን ማስተዋወቅና የምርጫ ክርክሮችን ያዘጋጃሉ። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ አሳታፊ እና አካታች እንዲሆን መገናኛ ብዙሃን እንደ ባለድርሻ አካል ሚናቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኦቢኤን) ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አንዋር ጀማል ተቋሙ ስርጭት በሚያከናውንባቸው ሁሉም ቋንቋዎች ምርጫውን በተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ሕዝቡ በቂ ግንዛቤ ጨብጦ በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲኖረው ከማድረግ አንጻር ሁሉንም የምርጫ ባለድርሻ አካላት ባሳተፈ መልኩ ጥረት እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይም የፖለቲካ ፓርቲዎች የየራሳቸውን ፖሊሲ፣ ስትራቴጂና አማራጭ ሃሳቦች ለሕዝቡ ማስተዋወቅ እንዲችሉ እድል ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ ተከታታይ የምርጫ ክርክር መድረኮችን በማዘጋጀት የምርጫ ማኑፌስቷቸውን እንዲያስተዋውቁ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። ተፎካካሪ ፓርቲዎች ተቋሙ ለስርጭት በሚጠቀምባቸው ቋንቋዎች አማራጭ ሃሳባቸውን ለሕዝብ ተደራሽ ማድረጋቸው የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋትና የምርጫ አውዱ እንዲጠናከር የጎላ ሚና እንዳለውም አስረድተዋል። ተቋሙ የምርጫ ዴስክ በማደራጀት በጠቅላላ ምርጫው ዙሪያ ሰፋ ያሉ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው ለጋዜጠኞች በምርጫ ሥነ-ምግባር፣ ደንቦችና ሕጎች ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ ወቅትና በድህረ ምርጫ ወቅት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ሊከተሏቸው በሚገቡ የሙያ ሥነ-ምግባርና የዘገባ አዘጋገብ ዘዴዎች ላይ ተከታታይ ሥልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑንም ገልጸዋል። ተቋሙ ከቴሌቪዥን ጣቢያው ባሻገር በኮርፖሬሽኑ ሥር ባሉ የኤፍ.ኤም ሬዲዮዎች በየዞኑ ጠቅላላ ምርጫውን የተመለከቱ ስራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት በምርጫ ሂደት የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ ነው
Mar 21, 2026 174
ዲላ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ):- ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት በምርጫ ሂደት የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ። "በኢትዮጵያ ምርጫ የማካሔድ ፋይዳዎች ለሀገር ግንባታ፣ ለሰላም፣ ለልማት እና ብልፅግና ያለው አንደምታ" በሚል መሪ ሃሳብ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች፣ በርካታ ምሁራን እና የተለያዩ ባለደርሻ አካላት በመድረኩ ተገኝተዋል።   በመድረኩ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ዲን፣ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ዘለቀ አርፍጮ፤ የምርጫ ሂደት ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። የምርጫ ሂደት የዜጎችን የፖለቲካ ተሳትፎና የመወሰን መብት የሚያጎናጽፍ እና ፓርቲዎችም ለሀገርና ህዝብ የሚጠቅሙ ፖሊሲና ስትራቴጂዎች የሚያመነጩበት ስለመሆኑ አስረድተዋል። በመሆኑም ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት በምርጫ ሂደት የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን የፖለቲካ ፓርቲዎች ፉክክርና የህዝቡ ተሳትፎ በጥሩ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን አንስተው ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ገልጸዋል።   የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ ዓለሙ (ዶ/ር)፤ በበኩላቸው በሁሉም ረገድ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማካሄድ የኢትዮጵያን ሀገረ መንግስት ግንባታ ማጽናት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በመሆኑም በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀሳባቸውን እንዲያንሸራሽሩ መድረክ በመፍጠር ዜጎች የጠራ ግንዛቤ ይዘው መምረጥ እንዲችሉ ሚዲያዎች ሃላፊነታቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል።   ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መጎልበት በዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳቦች እንዲሁም የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ የተለያዩ ሀሳቦችን እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ እየፈጠርን ነው - የሚዲያ ተቋማት
Mar 21, 2026 168
ሐዋሳ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ) :- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሀሳባቸውን ለህዝብ እንዲያቀርቡ መረጃን ተደራሽ በማድረግ ምቹ ሁኔታን እየፈጠሩ መሆናቸውን የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ ለማካሔድ ቀነ ቀጠሮ መያዙ የሚታወቅ ሲሆን ተሳታፊ ፓርቲዎችም የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ። በዚህም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያሏቸውን አማራጮችና የፓርቲ ፕሮግራም ለመራጩ ህዝብ የማስተዋወቅና የክርክር መድረኮችን በማካሔድ ላይ የሚገኙ ሲሆን በሀገሪቱ የሚገኙ የሚዲያ ተቋማትም ይህን ሃላፊነት እየተወጡ ይገኛሉ። ይህም መራጩ ህዝብ የፖለቲካ ፓርቲዎቹን የፖሊሲ አማራጭ ጠንቅቆ በማወቅ ትክክለኛ ውሳኔ እንዲወስን እድልን እንደሚፈጥር እሙን ነው። ኢዜአ የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እና የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሥራ ሃላፊዎችን በምርጫው ዙሪያ ለህዝቡ መረጃዎችን በማድረስ ረገድ ሃላፊነታቸውን ለመወጣት እያከናወኑት ስላለው ተግባር ጠይቋል።   የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ ዘላለም ገነሞ እንዳሉት ድርጅቱ ለምርጫው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የፖለቲካ ፓርቲዎች ይዘው የመጡትን የፖሊሲ አማራጮች እንዲያስተዋውቁ እያደረገ ይገኛል። በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች የሚንቀሳቀሱና በምርጫው የሚሳተፉ ፓርቲዎች በቴሌቪዥን የሚከራከሩበትን መድረክ በማዘጋጀት አመራጮቻቸውን እንዲያስተዋውቁ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ተናግረዋል። የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በዋና ጣቢያውና ባሉት ቅርንጫፎች በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በዲጂታል ሚዲያውና በጋዜጣ በ50 ቋንቋዎች ስለምርጫው ለህዝብ መረጃ እያደረሰ እንደሚገኝ አቶ ዘላለም ገልጸዋል። ድርጅቱ ከምርጫ ቦርድና ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው በቀጣይ ለፓርቲዎቹ በሚሰጠው የአየር ሰዓት ድልድል መሰረት ለማስተናገድ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።   የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈጻሚና የይዘት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አደገ አየለ ሲቢሲ በምርጫው የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚኖራቸው መድረኮች በመገኘት መረጃዎችን ለህዝቡ እያደረሰ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኮርፖሬሽኑ አጀንዳ በመቅረጽ ምርጫን በተመለከተ ከህብረተሰቡ ጋር ውይይቶችን በማድረግ አስተያየቶችን በመሰብሰብ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። ለማህበረሰቡ በሲዳምኛና በአማርኛ ቋንቋዎች ምርጫውን የተመለከቱ መረጃዎች እንዲደርሱት በቴሌቪዥንና በዲጂታል ሚዲያው እያሰራጨ ነው ብለዋል።
የተሻለ ሐሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች
Mar 21, 2026 182
ሠመራ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በዘንድሮው ምርጫ ለመሳተፍ የሚያስችለንን ካርድ በመጠቀም የተሻለ ሐሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ቀኑን እየጠበቅን ነው ሲሉ የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ነዋሪዎች መካከል ሃስና መሐመድ እንዳሉት፤ በዘንድሮው ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች እያካሄዱ ያሉትን የምርጫ ክርክር እየተከታተሉ ነው።   በዚህም የተሻለ ሐሳብ እያንፀባረቀ ያለውን ፓርቲ ለመለየት መቻላቸውን አንስተዋል። ሌሎቹ አስተያየት ሰጭዎች ዘሐራ ኢድሪስና ሃዋ ኢድሪስም፤ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸው ይበጀኛል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። ካርድ ያልወሰዱ ነዋሪዎች ካርድ በማውጣት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙም መክረዋል። በመራጭነት ለመሳተፍ የመጀመሪያው መሆኑን የገለጸው አብዱ ሁሴን በበኩሉ፤ በምርጫው ለመሳተፍ የምርጫ ቀኑ እስከሚደርስ እየጠበቀ መሆኑን ተናግሯል። እየተካሄዱ ያሉ የምርጫ ክርክሮችን እየተከታተለ መሆኑን ጠቁሞ፤ ይህም ሀገሬን ሊመራ የሚችለው ፓርቲ የትኛው ነው የሚለውን እንድለይ አስችሎኛል ብሏል። ምርጫ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የምንፈልገውን ፓርቲ የምንመርጥበት ልዩ ዕድል መሆኑን ተረድቼ የምርጫ ካርድ ወስጃለሁ ሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጭ ሐሰን መሐመድ ናቸው።
የምርጫ ካርድ በመያዝ ለኢትዮጵያ የተሻለ የሚሰራውን ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች
Mar 21, 2026 142
ሚዛን አማን፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ለኢትዮጵያ እድገት በንቃት መስራት የሚችለውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጁ ሆነናል ሲሉ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተናገሩ። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካታች፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ለማከናወን የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ሂደቶችን እየተገበረች ነው። ምርጫው በአሳታፊነቱ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችንም የሚያካትት በመሆኑ ኢዜአ ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር ቆይታ አድርጎ ተማሪዎቹ በምርጫው ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በትምህርት ላይ ቢሆኑም ያላቸውን ጊዜ በመጠቀም ካርድ ወስደው በሀገር ጉዳይ ላይ በድምጽ የመወሰን ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙበትም አረጋግጠዋል። የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ጌታቸው በላቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ እንደሚሳተፍ ገልጾ ለዚህም የምርጫ ካርድ በመውሰድ የተሻለ ሀሳብ የያዘ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀቱን ተናግሯል። በዚህም ካርዱን በመውሰድ የምርጫው ጊዜውን በጉጉት እየጠበቀች መሆኑን የተናገረችው ደግሞ ተማሪ ሰናይት ረዳይ ነች። እንደ ዜጋ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ግዴታችን በመሆኑ በእያንዳንዱ የምርጫ ሂደት ሕጉ በሚፈቅደው መንገድ ተሳትፈን የዴሞክራሲ ልምምድን ማጠናከር አለብን ብላለች። ተማሪ ታምሩ ገብረ ማርያም እና ተማሪ አቤል ሳምሶን በበኩላቸው በካርድ ድምጻችንን ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት ከወዲሁ እያደረግን ነው ብለዋል። ከመምረጥ ባሻገር የምንመርጠውን ፓርቲ ፖሊሲ ለይቶ መረዳትና ለኢትዮጵያ እድገት የተሻለ የሚሰራውን በቅድመ ምርጫ ጊዜ መለየት ይጠበቅብናል የሚል ሀሳብ አጋርተዋል። ሌሎች ተማሪዎችም በትምህርት የሚያውቁትን የምርጫ ሥነ ሥርዓት በተግባር ለማረጋገጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ተመዝግበው መውሰድና ለምርጫው መዘጋጀት እንዳለባቸውም አመልክተዋል።  
ነጻ የዓየር ሠዓት አጠቃቀም ለምርጫ ሂደት ዴሞክራሲያዊነት ወሳኝ ሚና አለው
Mar 21, 2026 134
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የነጻ የዓየር ሠዓት አጠቃቀም ለምርጫ ሂደት ዴሞክራሲያዊነት እና ፍትሐዊነት ወሳኝ ሚና እንዳለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን እና የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በተገኙበት፤ በፖለቲካ ፓርቲዎች ነጻ የዓየር ሠዓት ድልድልና አጠቃቀም ላይ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡   አቶ ተስፋዬ ንዋይ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ነጻ የዓየር ሠዓት ፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውንና ማኑፌስቷቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት ወሳኝ መድረክ ነው። ይህ አሠራር የምርጫ ሂደቱ ዴሞክራሲያዊ፣ ግልጽ እና ፍትሐዊ መሆኑን ከሚያሳዩ መገለጫዎች አንዱ ነው ብለዋል። ቦርዱ ከመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ጋር በመተባበር ነጻ የዓየር ሠዓት አጠቃቀምን የሚመራ መመሪያ አዘጋጅቶ ወደ ሥራ መግባቱንም አስታውቀዋል።   ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኃን የሚሰጣቸውን ነጻ የዓየር ሠዓት እና የጋዜጣ ዐምድ ለምርጫ ቅስቀሳ ሥራቸው በአግባቡ እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል። ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ከ18 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ዜጎች ለመራጭነት መመዝገባቸውንም አመላክተዋል።
ማህበራዊ
በመሬት ናዳ የተፈናቀሉ ወገኖችን ለማቋቋም የባለድርሻ አካላት ሚና እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ
Mar 21, 2026 110
አርባምንጭ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በጋሞ ዞን በመሬት ናዳ አደጋ የተፈናቀሉ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ሚና እንዲጠናከር የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ።   ኮሚሽንኑ በጋሞ ዞን በመሬት ናዳ አደጋ የተፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም በሚያስችሉ ሳይንሳዊ ጥናቶች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል። የኮሚሽንኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ በመሬት ናዳ አደጋ የተፈናቀሉትንና በአደጋ ስጋት ላይ የሚገኙ ሰዎችን መልሶ ለማቋቋም ተቋማቸው ሚናውን እንደሚወጣ ገልጸዋል። የበልግ ዝናቡ እንደሚቀጥል ጠቁመው፤ ተጨማሪ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት እንዳይደርስ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት በትኩረት እንዲሠራ አሳስበዋል።   የተለያዩ አጋሮች የዕለት ደራሽ ድጋፍ ከማድረግ ጎን ለጎን ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረጉ ጥረቶች እየተወጡ ያለውን አስተዋፅዖ እንዲያጠናክሩም ጠይቀዋል። ተፈናቃዮች በሚሰፍሩባቸው አካባቢዎች ትምህርት፣ ጤና፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ አገልግሎትን ጨምሮ የማኅበራዊና የመሠረተ-ልማት ሥራዎችን በማከናወን ከመንግሥት ጎን መቆም እንዳለባቸው አመልክተዋል።   የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት አመራርና የምግብ ዋስትና ኮሚሽን ኮሚሽነር ወገኔ ብዙነህ በበኩላቸው፤ ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ቦታዎች መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል።
የሐይማኖት አባቶች ችግሮችን በምክክር በመፍታት ለዘላቂ ሰላም መሥራት እንደሚገባ አስገነዘቡ
Mar 21, 2026 65
ገንዳ ውኃ፣ ጎንደር፤ መጋቢት12/2018 (ኢዜአ)፡- የአብሮነት እሴቶችን በማጎልበት ችግሮችን በምክክር በመፍታት ለዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ መሥራት እንደሚገባ የሐይማኖት አባቶች አስገነዘቡ። የገንዳ ውኃ ከተማ እስልምና ምክር ቤት ሰብሳቢ ሼኽ አሕመድ ኑርዬ እና የከተማዋ ነዋሪ ሼኽ ሙሀመድ ይማም፤ ለኢትዮጵያ አሁን ላይ ከምንም በላይ ሰላምና ልማት ያስፈልጋታል ብለዋል። የምንም ነገር መሠረቱ ሰላም መሆኑን አስገንዝበው፤ የሰላም ቁልፍ ያለው ደግሞ በእያንዳንዳችን ዕጅ ላይ በመሆኑ ለሰላምና ልማት መሥራት የጋራ ኃላፊነታቸን ነው ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል። የአብሮነት ዕሴቶችን በማጎልበት ችግሮችን በምክክር በመፍታት ለዘላቂ ሰላምና ልማት በመሥራት የጋራ ጥረታችን ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባልም ነው ያሉት። በተለያዩ ምክንያቶች ለቅራኔ የዳረጉ ሀገራዊ ችግሮችን በመቀራረብ በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምና ልማት ማምጣት እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን ማጥበቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የጎንደር ከተማ ነዋሪ ሀጂ ኡመር ዳውድ፣ ሼህ ከማል አደም እና ሰይድ ጀማል በበኩላቸው፤ የሐይማኖት አባቶች ከልዩነት ይልቅ የሚያቀራርቡ፣ ሰላምን የሚያጸኑ እና አንድነትን የሚያጠብቁ ተግባራት ላይ አተኩረን መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል። የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ሁሉንም ያሳተፈ የምክክር ሂደት መጀመሩ ለዘላቂ ሰላም ጥሩ መሰረት የሚያኖር ስለመሆኑም አስረድተዋል። በምክክር ችግሮችን ለመፍታት የሁላችንም ዝግጁነት ያስፈልጋል ሲሉም ገልጸዋል። ወጣቶች ስለ ሀገር ፍቅር፣ ሰላምና አብሮነት ዝግጁ ሆነው መሥራት እንዳለባቸውና የሐይማኖት መሪዎችም በዚሁ ልክ ማስተማር ይገባናል ነው ያሉት።
የሐይማኖት አባቶች ለሰላም ዕሴት መዳበር የሚያደርጉትን አስተዋጽዖ በይበልጥ ሊያጠናክሩ ይገባል
Mar 21, 2026 67
ባሕር ዳር፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር የሐይማኖት አባቶች የሰላም፣ አብሮነትና የመቻቻል ዕሴትን ለማጎልበት የሚያደርጉትን አስተዋጽዖ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተገለጸ። የከተማ አሥተዳደሩ “በመደመር ዕይታ የሐይማኖት ተቋማት መሪዎች ሚና” በሚል መሪ ሐሳብ በባሕር ዳር ከተማ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል። የአሥተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በዚሁ ወቅት፤ ቤተ ክርስቲያኗ በሀገር ግንባታ እንዲሁም ሰላም መስፈን ረገድ ድርሻዋን እየተወጣች ነው ብለዋል። የከተማዋን ሰላምና ፈጣን ልማት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የሐይማኖት መሪዎችና የምእመኑ ድጋፍ በይበልጥ ሊጠናከር እንደሚገባም አመላክተዋል። በቀጣይም በከተማ አሥተዳደሩ የሚገኙ የሐይማኖት አባቶች ለሰላምና አብሮነት የሚያደርጉትን አስተዋጽዖ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።   የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መላከ ሰላም ኤፍሬም ሙሉዓለም በበኩላቸው፤ ሰላም ለማንኛውም ሐይማኖታዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴ መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ቤተ ክርስቲያኗ በመደበኛ የጸሎትና የትምህርት ሥርዓቶቿ ሁሉ ለሰላም መስፈን ልዩ ትኩረት ሰጥታ እየሠራች መሆኑን አስረድተዋል። በቀጣይም ለሰላም የምታደርገውን ጥረት እንደምታጠናክር ጠቁመው፤ አሥተዳደሩ ከተማዋን ለማሳደግ እያደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅና የሚደገፍ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ተመራቂዎች እየተከናወኑ በሚገኘው ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት የድርሻቸውን ማበርከት ይጠበቅባቸዋል
Mar 21, 2026 134
ወልዲያ/ደብረ ብርሃን፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የቀሰሙትን ዕውቀትና ክህሎት ተጠቅመው በሀገሪቱ እየተከናወኑ በሚገኙ ሁለንተናዊ ልማቶች የድርሻቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ተመላከተ። ተመራቂ ተማሪዎቹ በበኩላቸው በተመረቁበት የሙያ ዘርፍ ህዝባቸውንና ሀገራቸውን በትጋት ለማገልገል መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አበበ ግርማ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የቀሰሙትን ዕውቀትና ክህሎት ሀገራችን እያከናወነች በምትገኘው ሁለንተናዊ ልማት የድርሻቸውን ማበርከት አለባቸው። ዩኒቨርሲቲው በማኔጅመንት፣ በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በቴክኖሎጂ እና በጤናው ዘርፍ 2 ሺህ 388 ተማሪዎችን ማስመረቁን ተናግረዋል። የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባና የዩኒቨርሲቲው የቦርድ አባል አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፤ ተመራቂዎች ከመንግሥት ሥራ ባሻገር የፈጠራ ክህሎታቸውን በመጠቀም የሥራ ዕድል ፈጣሪዎች ሊሆኑ እንደሚገባም አሳስበዋል። ከዚህ ባሻገርም በአገራቸው ሰላምና ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል። የማኔጅመንት ተመራቂው ጎበና ወንዴ በዩኒቨርስቲ ቆይታው ከቀለም ትምህርቱ ባሻገር የአንድነትና የመከባበር ባህልን ለማዳበር አስችሎኛል ብሏል። በተመረቀበት የሙያ ዘርፍም ሃገሩንና ህዝቡን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል መዘጋጀቱን ተናግሯል። ''ሙያዬ ከቴክኖሎጂ ዓለም ጋር ያዛመደኝ በመሆኑ ውጤታማ ስራ ለመስራት ትልቅ ተስፋ አድርጌያለሁ'' ያለችው ደግሞ በአይሲቲ ሙያ የተመረቀችው መስከረም አባተ ናት። ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ዕቅድ ስኬት ላይ የበኩሏን ለመወጣት ስልጠናው ጥሩ አጋጣሚን እንደፈጠረላትም ገልጻለች። በተመሳሳይም የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸው 1 ሺህ 800 ተማሪዎችን በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ አስመርቋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለስ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ተመራቂዎች ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በልማት፣ በሰላምና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ችግር ፈቺ ተግባራትን በማከናወን ሊያግዙ ይገባል። በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው በአዳዲስ ቴክኖሎጂ በተደገፈ የንድፈ ሀሳብና የተግባር ትምህርታቸውን ወስደው በተሻለ ብቃት ማጠናቀቃቸውን ተናግረዋል። ዛሬ ለምረቃ የበቁት በተለያዩ የትምህርት መስኮች 1 ሺህ 800 ተማሪዎች ሲሆኑ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ መቆየታቸውንም ጠቁመዋል። የዩኒቨርስቲው የቦርድ አባል አርቲስት አበበ ባልቻ እንዳለው፤ ተመራቂዎች በቆይታቸው ያገኙትን እውቀትና ክህሎት በመጠቀም በጥናትና ምርምር የታገዘ ችግር ፈቺ ተግባራትን ሊያከናውኑ ይገባል። በህክምና ላቦራቶሪ በከፍተኛ ውጤት የተመረቀው ቢተውልኝ ደባስ እንዳለው፤ በቆይታው ባገኘው እውቀት ሃገሩንና ህዝቡን በታማኝነት ለማገልገል መዘጋጀቱን ተናግሯል። ያስተማራትን ማህበረሰብ በቅንነት ለማገልገል መዘጋጀቷን የገለፀችው ደግሞ በከፍተኛ ውጤት የተመረቀችው ውዴ መላኩ ናት። በዩኒቨርስቲዎቹ ምረቃ ስነ-ስርዓቱ ተመራቂዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
በነዳጅ አቅርቦት ላይ የተፈጠረውን ዓለም አቀፍ ጫና ለመቋቋም በኃላፊነት መሥራት ይገባል
Mar 21, 2026 77
ሐረር፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በነዳጅ አቅርቦት ላይ የተፈጠረውን ዓለም አቀፍ ጫና ለመቋቋም በኃላፊነት መሥራት እንደሚገባ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ምሁር አስገነዘቡ። በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር ፍሬዘር ጥላሁን፤ በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ውስብስብ ችግር ለነዳጅ ገዢ ሀገራት ፈተና መሆኑን አንስተዋል። ስለዚህ ኢትዮጵያን ጨምሮ ነዳጅ ገዝተው የሚያስገቡ ሀገራት በቁጠባ መጠቀም እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። እንዲህ ዓይነት ዓለም አቀፍ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትም በኤሌክትሪክ ኃይል ልማትና ተጠቃሚነት ላይ ማተኮር እንደሚገም አመላክተዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ የልማት ጥረት ትልቅ ተስፋን የሠነቀ መሆኑን ጠቁመው፤ የአረንጓዴና ታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ማተኮሯ በጥሩ ተሞከሮነት የሚጠቀስ ነው ብለዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ ዘላቂ የልማት ጥረት እንዳለ ሆኖ ከነዳጅ ጋር በተያያዘ አሁን ያለውን ዓለም አቀፍ ችግር ለመሻገር በከፍተኛ ሀገራዊ አደራ እና የኃላፊነት ስሜት በትብብር መሥራት ይገባል ነው ያሉት።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት ሰጥቷል
Mar 21, 2026 91
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሚያስችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ራቢ (ኢ/ር) ገለጹ። የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ እና ጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ኢንቨስትመንትስ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።   ስምምነቱ በኢትዮጵያ በኢነርጂ ዘርፍ የክህሎት ልማትን፣ ኢኖቬሽን እና ዘላቂ የኢነርጂ ልማትን ለማሳደግ ያለመ እንደሆነ ተመላክቷል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ስምምነቱ ለዩኒቨርሲቲው ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ አለው። በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የንድፈ ሐሳብ ትምህርትን ከኢንዱስትሪው የተግባር ልምድ ጋር በማቀናጀት ለሀገር ግንባታ የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ የሚያካሂዳቸው ጥናትና ምርምሮች ለጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ፕሮጀክቶች ግብዓት ከመሆናቸው ባሻገር ከኩባንያው የሚገኘው ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ዕውቀት ለተማሪዎችና ለሀገር የኢነርጂ ዘርፍ ትልቅ አቅም ይፈጥራልም ነው ያሉት። ዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሚያስችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት መስጠቱን እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል።   የጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ኢንቨስትመንትስ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ፕሬዚዳንት ሱን ዦንግ እንዳሉት፤ ስምምነቱ በቻይና እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የኢንዱስትሪ እና የትምህርት ትስስር ለማሳደግ የሚያስችል ነው። በአካዳሚክ እና በኢንዱስትሪ መካከል የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ለመፍጠር ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነም አስረድተዋል። ጂ.ሲ.ኤል በኢነርጂ፣ ኢንጂነሪንግ፣ በቴክኒክ፣ በትምህርት፣ በምርምርና ፈጠራ ዘርፍ ጠንካራ አቅም እንዲሁም ውጤታማ የሰው ኃይል ለማፍራት እንደ ቁልፍ ማዕከል እንደሚያገለግል አስገንዝበዋል።
ዩኒቨርስቲው ለዲጂታል ኢትዮጵያ ስኬት በዘርፉ የተሻለ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት ድርሻውን እየተወጣ ነው
Mar 21, 2026 251
ሮቤ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ስኬት በዘርፉ የተሻለ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት ድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ ፈጠራና ኢንተርፕረነርሺፕ ላይ ያተኮረ ተግባር ተኮር ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል። ይህ ሥልጠና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ግብ ስኬት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው ተመላክቷል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።   በተለይም በባሌ እና ምስራቅ ባሌ ዞኖችና በምዕራብ አርሲ ዞን በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቴክኖሎጂ ዝንባሌ ያላቸውን ተማሪዎች በመመልመል የክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ በተለያዩ ጊዜያት በሚሰጡ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች የዜጎችን የሥራ ፈጣሪነት ባህል በሚያሳድግ መልኩ እንዲሰጡ መደረጉንም ገልጸዋል። በ2017 ዓ.ም በሀገር አቀፍ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውድድር ዩኒቨርሲቲውን ወክለው የቀረቡ ተማሪዎች አንደኛ ደረጃን በመያዝ ሽልማትና እውቅና ማግኘታቸው የዘርፉ ትኩረት ውጤት መሆኑን ለአብነት አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም አዲስ የፈጠራ ሀሳብና ግኝት ያላቸው ግለሰቦች በሥራቸው ስኬታማ እንዲሆኑና ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ተግዳሮቶችን እንዲረዱ የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑን አክለዋል። ዩኒቨርሲቲው ለዲጂታል ኢትዮጵያ ስኬት በዘርፉ ክህሎት የበለጸገ የሰው ኃይል ለማፍራት ድርሻውን መወጣቱን ይቀጥላል ነው ያሉት። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች ኢንተርፕራይዝ ከፍተኛ ባለሙያ ወይዘሮ ራሄል ደበበ በበኩላቸው፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ አገልግሎትን ከማዘመን ባለፈ የዜጎችን ተወዳዳሪነት እንደሚያሳድግ ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ተግባራትም ተቋማት አገልግሎታቸውን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር የዜጎችን ጊዜና ወጪ መቆጠብ መቻሉን አስታውሰዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተሻለ የፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ መሆኑንና የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መድረክም የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን ገልጸዋል።  
የትምህርት ዘርፉን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለመደገፍ ከተቀመጡ ወሳኝ ጉዳዮች አንዱ ደህንነቱ የተጠበቀ የትምህርትና ምዘና ስርዓት መዘርጋት ነው-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Mar 19, 2026 179
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2018 (ኢዜአ)፡-በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የትምህርት ዘርፉን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለመደገፍ ከተቀመጡ ወሳኝ ጉዳዮች አንዱ ደህንነቱ የተጠበቀና በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የትምህርትና ምዘና ስርዓት መዘርጋት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዛሬ ከክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ከከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ስርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ውይይት አካሂደዋል።   በዚህም እንደ ሀገር የተቋቋመው የፈተና ብሔራዊ ግብረ ሀይል በቅደመ ዝግጅት ስራዎች ያከናወናቸው ስራዎች የደረሱበትን የስራ ሂደት ገምግመዋል። የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ስርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል በለዋል። በሁሉም ክልሎች እና በሁለት የከተማ አስተዳደሮች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1452 ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሀሴ ወር ተጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ መግባባት ላይ ደርሰናል። በተጨማሪም ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ለመማሪያ የሚያገለግሉ እና ታትመው የተሰራጩ መጽሀፍት ወደ ትምህርት ቤቶች እንዲሰራጩ እንዲሁም ከቅድመ አንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል ድረስ የሚያገለግሉ መጽሀፍት እስከ መጪው መስከረም ድረስ ታትመው ወደ ትምህርት ቤቶች እንዲሰራጩ አቅጣጫ አስቀምጠና ነው ያሉት። በመጨረሻም የዲጂታል ትምህርት ፈተና ምዘና ስርዓቱ ከሀገራዊ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መርሆዎች ጋር መጣጣሙን በማረጋገጥ፤ የተጀመረውን ዝግጅት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ መግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
በአማራ ክልል የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የሕዝብ እርካታን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ ይጠናከራል
Mar 18, 2026 270
ባሕር ዳር፤መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ዘመኑን በሚመጥን መልኩ በቴክኖሎጂ ታግዞ ተደራሽ እንዲሆን የተጀመሩ ስራዎች እንደሚጠናከሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ። ''ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ሀሳብ የክልሉ የመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ፍኖተ ካርታ ትውውቅ መድረክ በባሕር ዳር ከተማ ተካሄዷል።   ፍኖተ ካርታው በክልሉ የሚገኙ የመንግሥት ተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመ መሆኑም ተመልክቷል። ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በመድረኩ ላይ እንዳሉት፤ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የሕዝብ የመገልገል ፍላጎት መሠረት ያደረገ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ የመንግሥት ቀዳሚ ተግባር ነው። ፍኖታ ካርታው በክልሉ የመንግሥት ሠራተኞች የብቃት ምዘና ሥርዓትን በመገንባት ውጤታማ አገልግሎት አሰጣጥን ለማረጋገጥ ያግዛል። በተጨማሪም የመንግስት ሰራተኛውን የማስፈጸም አቅም ማሳደግ፣ ብዝሃነትንና አካታችነትን ያረጋገጠ ሲቪል ሰርቪስ መገንባት እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ዲጂታል የሥራ አካባቢን መፍጠር ዋና ዋና የሪፎርሙ አቅጣጫዎች መሆናቸውን አስረድተዋል። ተቋማትም ፍኖተ ካርታውን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የአገልግሎት ጥራትን፣ ፍጥነትን፣ ፍትሐዊነትንና እርካታን በሚያረጋግጥ መልኩ ሊሠሩ እንደሚገባም አሳስበዋል። ለዚህም ሲቪል ሰርቫንቱ የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመታጠቅ፣ በላቀ ብቃት፣ ዕውቀትና ክህሎት ታግዞ ሪፎርሙን ሊተገብር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።   የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥና ኢትዮጵያን ለማሻገር የሚያስችል የሲቪል ሰርቪስ ፖሊሲ ተቀርጾ ወደ ትግበራ መገባቱን ገልጸዋል። ፖሊሲው ሀገራዊ ዕውቀትንና ልምድን መሠረት ያደረገ በመሆኑ በፍጥነት ለውጥ ለማስመዝገብ እንደሚያስችል ጠቁመዋል። የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በ36 ማዕከላት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ፤ ይህም ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት እያስቻለ መሆኑን አስረድተዋል። የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ባንችአምላክ ገብረማርያም በበኩላቸው፤ ሪፎርሙ ቀደም ሲል በተቋማት ይስተዋሉ የነበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።   መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተግባራዊ በተደረገባቸው ከተሞች የሕዝብ እርካታን 97 በመቶ ማድረስ መቻሉን የገለጹት ኃላፊዋ፤ ይህንን ውጤት ለማስፋት የሪፎርም ፍኖተ ካርታውን በላቀ ትብብር መተግበር እንደሚገባም አሳስበዋል። በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ በመጀመሪያው ምዕራፍ ወደ ትግበራ ከሚገቡ የተለያዩ የክልል ተቋማት ጋር የሰነድ ርክክብ ተከናውኗል።
ስፖርት
በ3000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ አትሌት ባለሽኝ ባወቀ እና አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ አራተኛና ስድስተኛ ወጥተዋል 
Mar 21, 2026 90
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ21ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ማምሻውን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉባቸው የፍጻሜ ውድድሮች ተደርገዋል።   በ3000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ አትሌት ባለሽኝ ባወቀ 9 ደቂቃ ከ00 ሴኮንድ ከ26 ማይክሮ ሴኮንድ አራተኛ ወጥታለች። በውድድሩ ላይ የተሳተፈችው ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ አትሌት አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ 9 ደቂቃ ከ02 ሴኮንድ ከ41 ማይክሮ ሴኮንድ ስድስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ጣልያናዊቷ አትሌት ናዲያ ባቶክሌቲ 8 ደቂቃ ከ57 ሴኮንድ ከ64 ማይክሮ ሴኮንድ አንደኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች። አሜሪካዊቷ ኤሚሊ ማክካይ ሁለተኛ እና አውስትራሊያዊቷ ጄሲካ ሁል ሶስተኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን አጠናቀዋል።   በወንዶች የ3000 ሜትር የፍጻሜ ውድድር አትሌት አዲሱ ይሁኔ 7 ደቂቃ ከ38 ሴኮንድ ከ60 ማይክሮ ሴኮንድ ስምንተኛ ወጥቷል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ጌትነት ዋለ 7 ደቂቃ ከ40 ሴኮንድ ከ21 ማይክሮ ሴኮንድ 12ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። የታላቋ ብሪታኒያ አትሌት ጆሽ ኬር 7 ደቂቃ ከ35 ሴኮንድ ከ56 ማይክሮ ሴኮንድ አንደኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳሊያ አግኝቷል። አሜሪካዊው ኮል ሆከር ሁለተኛ ሲወጣ ፈረንሳዊው ያን ሽሩብ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። በፖላንድ ቶሩን ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። ሻምፒዮናው ነገ ይጠናቀቃል።
አካባቢ ጥበቃ
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው - አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ
Mar 21, 2026 76
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሌሎች ሀገራት ትልቅ መነሳሳትን የሚፈጥርና ምሳሌ የሚሆን ፕሮጀክት ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከማጠናከር ባለፈ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው። ይህ መርሃ ግብር በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነ ግዙፍ የደን ልማትና የተፈጥሮ ጥበቃ ዘመቻ ሲሆን የካርቦን ልቀትን በመቀነስ ረገድም በምሳሌነት ተጠቃሽ ነው። ሀገሪቱ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የተፈጥሮ ሥርዓት እንድትገነባ እያገዘም ይገኛል።   በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዮሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፔቴ ለኢዜአ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የአረንጓዴ አሻራ ፖሊሲ እጅግ የሚደነቅ ጥረት ነው ብለዋል። አረንጓዴ አሻራ ለሌሎች ሀገራትና መሪዎች አርአያ የሚሆን ተሞክሮ እንደሚሆን ጠቁመው ይህ ተግባር ሁላችንም በጋራ እንድንሰራ ያበረታታናል ነው ያሉት። የሀገራት መሪዎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት እየመጡ ያሉ ተግዳሮቶችን ለዜጎች በግልጽ ማሳወቅ እንዳለባቸውና ይህም ዜጎች ለመፍትሄው እንዲሰሩ ያደርጋል ሲሉ ገልጸዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2027 የሚካሄደውን 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ መመረጧን አምባሳደሩ አድንቀዋል። ኮሎምቢያ እ.ኤ.አ. በ2024 የኮፕ 16 ጉባኤን ማስተናገዷን አውስተው ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን በምታዘጋጅበት ወቅት ሀገራቸው ያካበተችውን ልምድ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። አምባሳደሩ አክለውም የኮሎምቢያን ተሞክሮና የኢትዮጵያን የወደፊት ራዕይ በማጣመር፣ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት ይሰራሉ ብለዋል።
የዜጎችን የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ለሚያሻሽሉ መመሪያዎች ተፈፃሚነት ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል
Mar 21, 2026 89
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የዜጎችን የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ የሚያሻሽሉ መመሪያዎችን በማውጣት ለተግባራዊነታቸው ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና የአካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከፋርም አፍሪካና ኤስ.ኦ.ኤስ ሳህል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ትግበራ ላይ ትኩረት ያደረገ የውይይት መድረክ አካሂዷል፡፡ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የባለድርሻ ተቋማትን ትብብር በማጠናከር በደንብ ቁጥር 545/2016 በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ሥርዓትን ይከታተላል፤ ይቆጣጠራል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ተፈጥሮ የቸራትን ዕምቅ የብዝኅ ህይወት ሃብት በሚገባት ልክ ጥቅም ላይ እያዋለች እንዳልሆነ ገልጸዋል። ለዚህም የውሃና የየብስ የሥነ-ምኅዳር ጸጋዎች ለሀገር የኢኮኖሚ ጥቅም ለማዋል የሚስችል "የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ አዋጅ ቁጥር 140/2018" ተግባራዊ መደረጉን አስታውቀዋል። ምክር ቤቱም ከመንግስተና የዘርፉ ተዋናዮች ጋር የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረኮችን በማዘጋጀት ግብዓት ታክሎበት አዋጁን በማፅደቅ ሥራ ላይ እንዲውል መደረጉን ተናግረዋል። በዚህም የዜጎችን የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ለማሻሻል የሚረዱ የማስፈጸሚያ ደንቦችና መመሪያዎች መውጣታቸውንና ተፈፃሚነ መሆናቸውን ጥብቅ ክትትል እንደሚደረግ አንስተዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ንጉሱ ለማ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቀናጀ የሥነ-ምህዳር አገልግሎት የክፍያና የሕግ ማዕቀፍ እንዳለነበረ ገልጸዋል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ሥርዓተ ምኅዳር ዘላቂነት ለማስጠበቅ የመንግስትና የባለድርሻ ተቋማትን ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ አዋጅ ቁጥር 140/2018 መፅደቁን ተናግረዋል። የአገልግሎት ክፍያ የአሰራር ሥርዓቱም የኢኮኖሚ ዕድልን በመፍጠርና ለአገልግሎቱ አቅራቢዎች ዘላቂ ዋስትናን ይፈጥራል ብለዋል፡፡ አዋጁን መነሻ በማድረግ የዘርፉን ተዋናዮች ተሳትፎ ማሳደግ የሚያስችል የማስተግበሪያ መመሪያ መዘጋጀቱን አስረድተዋል። የፋርም አፍሪካ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሸዊት አማኑኤል፤ ኢትዮጵያ ደኖችን በመንከባከብ የበካይ ጋዝ ልቀትን በመቀነስ ለዓለም የከባቢ አየር ሥነ ምህዳር ገንቢ ሚና እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ደንን በመንከባከብ በአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ በሚበረክቱት አስተዋፅኦ ልክ ሳይንሳዊ ጥናትና ኦዲት ተካሂዶ ገቢ ማመንጨት መጀመሩን አንስተዋል። የሥርዓተ ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ አዋጅ በባሌ አካባቢ የተጀመረውን በሌሎች አካባቢዎች ለማስፋት በር የሚከፍት መልካመ ዕድል መሆኑንም ተናግረዋል፡፡  
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የደን ሽፋንን በማሳደግ ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እያበረከተ ይገኛል
Mar 21, 2026 64
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የደን ሽፋን በማሳደግ ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እያበረከተ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ። የፌዴራልና የክልል መንግስታት የግብርና ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ''የመደመር መንግሥት የተፈጥሮ ሃብት ዕይታ'' በሚል መሪ ሃሳብ የዓለም አቀፍ የደን ቀን የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡   በመድረኩ የግብርና ሚኒስትር አቶ አዲስ አረጋ፤ የመደመር መንግሥት ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሰጠው ትኩረት የተፈጥሮ ሃብቶችን በማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማበርከት ያስቻለ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። በዚህም ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደግ እንደተቻለ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የተራቆተ የመሬት ገፅታ በደን በመሸፈን የአፈር መሸርሸርና የሥነ-ምኅዳር ደኅንነትን መጠበቅ ያስቻለ ውጤት እየተገኘ መሆኑንም አንስተዋል። ቡናን ጨምሮ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞች የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እያበረከቱ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በቀጣይም የማህበረሰቡን የደን ጥበቃ ግንዛቤ በማሳደግና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የደን ልማት ስኬትም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቀነስ የግብርና ምርታማነትን እያሳደገ እንደሚገኝ አብራርተዋል። ለአብነትም ከሰባት ዓመታት በፊት ወደ ውጭ ይላክ የነበረን 230 ሺህ ቶን የቡና ምርት አሁን ላይ ወደ 475 ሺህ ቶን በማሳደግ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ማግኘት እንደተቻለ አንስተዋል።   የኢትዮጵያ ደን ልማት ዋና ዳይሬክተር ከበደ ይማም በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ የደን ሃብት ልማት መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እያስገኘ ነው ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬታማነትም ከክልልና ባለድርሻ ተቋማት ጋር በቅንጅት መሰራቱን አንስተዋል።   የአረጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር)፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያስገኘውን ስኬትና ቀጣይ ሥራ የሚዳስስ የመነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል። ይህም የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የዓባይ ተፋሰስ ወረዳዎችን የተራቆተ የመሬት ገፅታ በደን በመሸፈን የከርሰና የገፀ ምድር ሃብቶች ላይ ዘርፍ ብዙ ጠቀሜታ እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
የተፈጥሮ ሃብት አገልግሎት አቅራቢዎች ለሥነ-ምኅዳር ደኅንነት በይበልጥ ሊተጉ ይገባል
Mar 21, 2026 69
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የተፈጥሮ ሃብት አገልግሎት አቅራቢዎች የአካባቢ ጥበቃ ባህልን በማሳደግ ለሥነ-ምኅዳር ደኅንነት ይበልጥ ሊሠሩ እንደሚገባ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አሳሰበ። ባለሥልጣኑ ከፋርም አፍሪካ እና ኤስ.ኦ.ኤስ ሳህል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ትግበራ ላይ ትኩረት ያደረገ የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።   በዚሁ ወቅትም የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ንጉሡ ለማ፤ ተቋማቸው የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ ሥርዓትን የመከታተልና የመቆጣጠር ኃላፊነት እንዳለበት ገልጸዋል። በዚህም የኢትዮጵያን ሥርዓተ-ምኅዳር ዘላቂነት ለማስጠበቅ የመንግሥትና የባለድርሻ ተቋማትን ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት ክፍያ አዋጅ ቁጥር 140/2018 መጽደቁን አስረድተዋል።   የሥርዓተ-ምኅዳር የአገልግሎት ክፍያ የአሠራር ሥርዓቱም ለተጠቃሚዎችና አገልግሎት አቅራቢዎች ምቹ የክፍያ መፈጸሚያ ሁኔታ እንደፈጠረ አረጋግጠዋል። ይህም የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎት አቅርቦትን በማሻሻልና ዘላቂነት እንዲኖረው ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል ብለዋል።   አዋጁም ከዚህ በፊት ክፍያ ያልተተመነላቸው የሥርዓተ-ምኅዳር አገልግሎቶች ላይ የዋጋ ተመን በማስቀመጥ የኢኮኖሚ ዕድልን እንደሚፈጥር አስረድተዋል። ለአዋጁ ገቢራዊነት የዘርፉ ተዋንያን ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ ባለሥልጣኑ ለአዋጁ ማስፈጸሚያነት የሚየገለግሉ መመሪያዎች ማዘጋጀቱን አስታውቀዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ሀገራት የሴቶች መብቶችን የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባቸዋል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Mar 9, 2026 199
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የሴቶች መብቶች እና የሥርዓተ ጾታ እኩልነነት የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን እንዲወስዱ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጥሪ አቀረቡ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። "መብቶች፣ ፍትሕ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሐሳብ ነው። የአፍሪካ ኀብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።   በመልዕክታቸውም፤ ቀኑ የአፍሪካ ሴቶች እና ልጃገረድ ስኬቶችን የምናከብርበት፣ ሴቶችን ማብቃት እና ጥበቃ ላይ የገባናቸውን ቃል ኪዳኖች ዳግም የምናድስበት ነው ብለዋል። ሴቶች በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ከአመራር ሰጪነት እስከ ቴክኒካዊ ቦታዎች ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም አመልክተዋል። የሥርዓተ ጾታ እኩልነት የተቋሙ ሥራ ማዕከል መሆኑንም አስረድተዋል። የአፍሪካ ኅብረትም ቀኑን እያከበረ ሲሆን፤ የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር በአፍሪካ የሴቶችን መብቶች የሚደግፉ ቁልፍ ማዕቀፎችን በዚሁ ወቅት አንስተዋል። ለአብነትም የአፍሪካ ኅብረት የሰው እና ዜጎች መብቶች ቻርተር የሴቶች መብቶች የሕግ ማዕቀፍ፣ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) እና የሴቶችና ልጃገረዶች ጥቃትን ማስቆም ያለመውን የኅብረቱ ን ኮንቬንሽን በማሳያነት ጠቅሰዋል። የኮንቬንሽኑ ወደ ትግበራ መግባት ትልቅ ስኬት እንደሆነ ገልጸው፤ ሀገራት በሕግ አውጪ ምክር ቤት ማዕቀፉን በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲያስገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ሊቀ መንበሩ የሥርዓተ ጾታ እኩልነት እና የልማት የትኩረት መስኮች ቁርኝት እንዳለውም አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የ2026 ትኩረት በሆነው ውኃ እና ንጽህና ጋር በተያያዘ፤ ሀገራት የሴቶችን ጫና የሚያቃልሉ እና ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን እንዲያከናውኑም ጥሪ አቅርበዋል።
በቀጣናው የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው -ኢጋድ
Mar 8, 2026 191
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂን ጨምሮ በቀጣናው የሴቶችን የአመራርና ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው። "መብቶች፣ ፍትህ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሴቶችን ቀን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፏል። ኢጋድ ለሴቶች አመራር ሰጪነት፣ አይበገሬነት እና በቀጣናው ሰላም፣ ብልጽግና እና ለውጥ ለማምጣት እያበረከቱት ላለው አስተዋጽኦ ክብር እና እውቅና እንደሚሰጥ ገልጿል። በኢጋድ ሴቶች በቀጣናው አመራር ሰጪነት ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። የኢጋድ የሰላም፣ ግብርና፣ ዲጂታል ደህንነት፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና መሬት አስተዳደር ፎረሞች እንዲሁም የኢጋድ የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂ ጨምሮ የተለያዩ ኢንሼቲቮች እየተገበረ መሆኑን አመልክቷል። የሴቶች ድምጽ እንዲሰማ እና መሉ ተሳትፏቸው እንዲረጋገጥ የሚያግዙ መድረኮችን መፍጠሩን ነው የኢጋድ ሴክሬተሪያት በመረጃው ያስታወቀው።
ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በሰላምና ደኅንነት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Mar 5, 2026 222
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢጋድ የሰላም እና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ውይይቱን ያደረጉት የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁን (ዶ/ር) በመወከል ነው። ውይይቱ ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም፣ ደኅንነት እና መረጋጋት ላይ ያላቸውን የጋራ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው። ሁለቱ ወገኖች የጋራ የተግባር ምላሽ ለመስጠት እና ስትራቴጂካዊ ትብብራቸውን ለማጎልበት ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3204
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ 
Mar 2, 2026 322
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል።   የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 376
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።      
   የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 359
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን።   የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው።   የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል።   የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት።   የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 21, 2026 171
ከመጋቢት 6 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ማሳሰቢያ በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ስለዚህ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በኃላፊነት ልንጠቀም ይገባል ሲሉ ያሳሰቡት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ባሳለፍነው ሳምንት … ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል ፕሬዚዳንት ታዬ ያስጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባሳለፍነው ሳምንት የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑን ገልጸው፤ የሕይወት ምሉዕነት የሚረጋገጠው ካለው ላይ ቆርሶ በመስጠት መሆኑን አስገንዝበዋል። ለተቸገሩ መድረስና ለወገን መቆም ትልቅ የመንፈስ ዕርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ መጠናከር እንዳለበትም አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ የተወያዩት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጉብኝት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በእንዶዴ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ እና በኤ ኤም ጂ (AMG) - እንዶዴ የባቡር መሥመር ፕሮጀክቶች ላይ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። እነዚህ በራስ ዐቅም የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነታችንን ከማሻሻል ባለፈ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ያጸናሉ ሲሉም በዚሁ ወቅት በአጽንዖት ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ጋር በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ መሥተዳድሮች፣ ከከተማ አሥተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ሥርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ሥርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1 ሺህ 452 ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሐሴ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ረመዳን ወር ተጠናቅቆ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት የተከበረው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ለበዓሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች የፌደራል፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። #ባሳለፍነው_ሣምንት #ኢዜአ
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 21, 2026 76
በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ (በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት ስትወጥን የቀደመ ወረቷን፤ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶቿን ይዛ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን ቀረጸች። ይህን ዕውን ለማድረግ ስትዘይድም የሕዝቧን የፋይናንስ፣ የዕውቀት እና የጉልበት ዐቅም በመደመር መጠቀምን ሻተች። በዚህም መሠረት በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶችን አስመዘገበች። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። በኢዜአ ዐይን …! ✍️ ገበታ ለሸገር በአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻዎችና መናፈሻዎችን ለማልማት በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረገው ገበታ ለሸገር ኢኒሼቲቭ፤ ከእንጦጦ ተራራ እስከ አቃቂ ወንዝ ያለውን የሚሸፍን ነው። የሚሠራበትን ገንዘብ ለማሰባሰብም የገበታ ለሸገር የእራት ምሽት በዳግማዊ አጼ ምኒልክ የግብር አዳራሽ ተዘጋጀ፤ ባለሀብቶች፣ የንግድ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ጨምሮ ዓለም አቀፍና አኅጉራዊ ድርጅቶችም ተሳትፈዋል። ኢኒሼቲቩ አንድነት ፓርክን ጨምሮ የእንጦጦ መናፈሻንና ሌሎች የተለያዩ መዲናዋን ያስዋቡ በረከቶችን ችሯል። ይህም የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት በርካታ ቱሪስቶችን ከመሳብ ባለፈ፤ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለምጣኔ ሃብት ዕድገት ጉልኅ አስተዋጽዖ አበርክቷል። ለዚህ ሁሉ ስኬት መነሻ የሆኑትን ጉዳዮች ያስጀመሩትም ያስፈጸሙትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በገበታ ለሸገር የተገኙ ውጤቶችን መነሻ በማድረግ ገበታ ለሀገር የተሰኘውን ኢኒሼቲቭ አበሠሩ። ✍️ ገበታ ለሀገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነሐሴ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻን ለማልማት ያለመ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አዘጋጅተዋል። ይህም በአዲስ አበባ ከተሠራው ገበታ ለሸገር ቀጥሎ የተከናወነ ነው። በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የገበታ ለሀገር ዓላማ የተለያዩ አካላትን በማሳተፍ የቱሪስት መስኅብ የሚሆኑና የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ አካባቢዎችን ማዘጋጀት መሆኑን አስገንዝበዋል። በገበታ ለሀገር መርሐ-ግብር ባለሀብቶችን ጨምሮ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ 3 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህን ለማሳካት የሀገሪቱን ባለሃብቶች፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች በተለያዩ መርሐ-ግብሮች የተሳተፉበት የገቢ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ውጤታማ ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገበታ ለሀገር ውጥን፤ እንደ ሀላላ ኬላ፣ ጨበራ ጩርጩራ፣ ወንጪ እና ጎርጎራ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና የተፈጥሮ ሀብቶችን አጉልተው በማሳየት ይበል ያሰኘ ውጤት አስመዝግቧል። ✍️ ገበታ ለትውልድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2015 ዓ.ም ገበታ ለትውልድ የተሰኘ ኢኒሼቲቭ ይፋ ያደረጉ ሲሆን፤ ይህም ተጨማሪ መዳረሻዎች እንዲለሙ አስችሏል። በዚህ ኢኒሼቲቭ ሥር በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በአፋርና ሶማሌ ክልሎች የመዳረሻ ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል፤ እየተከናወኑም ነው። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዳሴ ግድብ አካባቢና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የፕሮጀክቱ አካል የሆኑ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራዎች እየለሙ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውን የሸበሌ ሪዞርት በይፋ መርቀዋል። እያንዳንዱ የሪዞርቱ ገጽታ የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ባህላዊ ሐብት የሚያንፀባርቅ ነው። ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በሚደረገው ጉዞ ትልቅ ታሪካዊ እጥፋት እንደሆነም ተገልጿል። ሎጎ ሐይቅ ሪዞርትም ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመረቀ ሲሆን፤ ለጎብኚዎች የማይረሳ ትውስታን የሚሰጥ እጅግ ማራኪ ቦታ ሆኖ ቀርቧል። ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለመሆን ያላትን ቁርጠኝነትና ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ቋሚ ምስክርም ነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት። የቱሪዝም ልማቱን ከተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ፣ ከዘላቂነትና ከአካታችነት ጋር በማቀናጀት፤ ሪዞርቱ የወሎ ሕዝብ ያለውን ጥልቅ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ዕሴት ለዓለም ማኅበረሰብ የሚያስተዋውቅበት ሰፊ ገበታ ሆኖ ያገለግላል። ታሪካዊ ቦታዎችና የሀገር መገለጫ መሠረተ-ልማቶች ብሔራዊ ትርክቶችንም የሚገነቡ ናቸው። በአጠቃላይ እነዚህ ሁሉ ጥረቶች ለአካባቢ ጥበቃ ቅድሚያ በመስጠት ብሎም በየአካባቢው የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል። የቱሪዝም ዘርፉን ለማጎልበት፣ ብዙ ጎብኚዎችን ለመሳብ፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማጠናከር፣ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው። እንዲሁም ነባር ቅርሶችን በማደስና በመጠገን ለትውልድ ለማሻገር ደማቅ ዐሻራ አሳርፈዋል። በሌላ በኩል የቱሪዝም መዳረሻዎችን ማልማት የመንግሥት ብቻ እንዳልሆነ ዐሳይተዋል። ባለሀብቶችና ሌሎች የማኅበረሰብ ክፍሎችም ሀገራቸውን የመሥራት ሚና እንደሚጠበቅባቸው አሥተምረዋል። ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት ብሎም በርካታ የሥራ ዕድሎች በመፍጠር በኢኮኖሚው ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በኢትዮጵያም ቱሪዝም መንግሥት ላስጀመረው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የማዕዘን ድንጋይ ነው። ከአምስቱ ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎችም አንዱ የሆነው ለዚህ ነው። መሠረተ-ልማቶች ከሚገነቡባቸው ጡቦች ባለፈ የነገን ሀገራዊ ማንነት፣ ራዕይ እና መዳረሻን ይበይናሉ። ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ እንኳንም ታሰቡ፤ እንኳንም ተሳኩ። ይህ ባይሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ተጨማሪ መዳረሻ ባላገኘች ነበር።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 14, 2026 1351
ከየካቲት 29 - መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ✍️ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምሥራቅ ኢትዮጵያ • ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተመልክተዋል። ማዕከሉ በውስጡ 10 ተቋማት ይዞ 73 የሚሆኑ አገልግሎቶችን ለዜጎች እየሰጠ መሆኑንም ገልፀዋል። ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል • በተመሳሳይ በድሬዳዋ የተስማሚነት ምዘና ድርጅትን ጎብኝተዋል። ድርጅቱ ዓለም አቀፍ የአሠራር ሥርዓትን በመከተል ለአምራቾች፣ ለአገልግሎት ሰጪዎች፣ ለላኪዎች፣ ለአስመጪዎች፣ ለተቆጣጣሪ መሥሪያ ቤቶች፣ ለምርምር ተቋማትና ለሸማቹ ማኅበረሰብ የምርትና አገልግሎቶች የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም ተናግረዋል። • የድሬዳዋ የኮሪደር ልማትንም የጎበኙ ሲሆን፤ የኮሪደር ልማቱ ምቹ የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች፣ የተሻሻለ የአካባቢ ውበትን እና ጥራታቸውን የጠበቁ የማኅበረሰብ መሰብሰቢያ ስፍራዎች በድሬዳዋ ዕውን እንዲሆኑ ማስቻሉን አስረድተዋል። • ከድሬዳዋ ነዋሪዎች ጋርም የረመዳን ኢፍጣር መርሐ-ግብር ያከናወኑት ባለፈው ሳምንት ነው። • በድሬዳዋ የሚገኘውን እመርታ ቤተ-መጻሕፍትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጎብኝተዋል። ቤተ-መጻሕፍቱ በአንድ ጊዜ ለ1 ሺህ ሰው አገልግሎት መስጠት እንደሚችል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። • በሳምንቱ መጀመሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሐረሪ ክልል ሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተሠራውን የገጠር ኮሪደር ሥራ ተመልክተዋል። የአካባቢው ነዋሪ በንቃት የተሳተፈበት የገጠር ኮሪደር ሥራ፤ ባሕላዊ የግንባታ ዘዴን፣ የተደራጀ ዕቅድ እና ተግባራዊ የአሠራር ውጤት ያሳየ መሆኑን አብራርተዋል። • የቁንድዶ ተራሮችንም ጎብኝተዋል። • በሐረር ከተማ የተቋቋመውን መሶብ የአንድ ማዕከልም ተመልክተዋል። ማዕከሉ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል አቀናጅቶ የማቅረብ ሀገር ዐቀፍ መርሐ-ግብር አካል መሆኑንም አስገንዝበዋል። • በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን መልካ በሎ ወረዳ የሚገኘውን ናሲኦል ዋሻም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት ጎብኝተዋል። • ከሐረር ከተማ ነዋሪዎች ጋርም የረመዳን ኢፍጣር አካሂደዋል። ✍️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሹመት መስጠታቸው • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ ሌ/ጄኔራል አሥራት ደኔሮን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር፣ ረዳት ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድን እና አቶ ኤርዚቅ ኢሳን የአዲስ አበባ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነሮች አድርገው የሾሙት ባሳለፍነው ሳምንት ነው። ✍️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከልዑካቸው ጋር በጅቡቲ የቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሐመድ እና የጅቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ዑማር ጊሌ በተገኙበት ውይይት አድርገዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥራ ጉብኝታቸውን ቀጥለውም ወደ ተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ያቀኑት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በዚሁ ወቅትም ከፕሬዚዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተወያይተዋል። ውይይታቸውም በሀገራቱ መካከል ለረጅም ዘመናት የቆየውን ወዳጅነት በማጎልበት፤ ትብብር እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር። ✍️ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ከዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ኅብረት ጋር መምከራቸው • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ባዘጋጀው የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይ ታድመዋል። በዚሁ ወቅትም የሁሉም እምነት፣ ባህልና ሥርዓት የሚከበርባት ኢትዮጵያን መገንባት የመደመር መንግሥት ተልዕኮ መሆኑን ገልጸዋል። • ከዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ኅብረት ዳይሬክተር ኮስማስ ዛቫዛቫ (ዶ/ር) ጋር በዲጂታል ልማት ያለ ትብብርን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት ያደረጉት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በቀጣይም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ከግብ ለማድረስ እና ትብብራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር በጀመርናቸው እና በሌሎች አዳዲስ ዘርፎች ዙሪያ በጋራ ለመሥራት ተስማምተናል ሲሉም ገልጸዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። • በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አዘጋጅነት በተከናወነው የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይም የታደሙ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት “ጎረቤቱ ርቦት እርሱ ጠግቦ የሚያድር ከኛ አይደለም” የሚለው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) አስተምኅሮ፣ ለሰው ልጅ ክብር መስጠትን፣ ርኅራኄን፣ የጋራ ደስታንና አብሮነትን በተግባር መተርጎም እንዳለብን የሚያሳይ ኅያው የሕይወት ስንቅ ነው ብለዋል። ✍️ የመሬት ናዳና ጎርፍ አደጋ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ • ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በተከሰተ የመሬት ናዳ እና ጎርፍ የዜጎች ሕይወት አልፏል፤ በንብረት ላይም ውድመት ደርሷል። ይህን ተከትሎም ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች የሐዘን መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል። • ከዚሁ ጋር በተያያዘ በጋሞ ዞን በመሬት ናዳ አደጋ የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም ከፌደራል መንግሥት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ከበደ ያስታወቁት ባሳለፍነው ሳምንት ነው። እስካሁንም በአደጋው ሳቢያ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስና መልሶ ለማቋቋም ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ በተቀናጀ መንገድ እየተሠራ መሆኑን አረጋግጠዋል። መላው የኢትዮጵያ ሕዝብም ለወገኑ ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ✍ ምክር ቤቱ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ማወጁ • የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት ምክንያት ሕይወታቸው ያለፉትን ዜጎች በማስመልከት ብሔራዊ የሐዘን ቀን ዐውጇል። በዚህም መሠረት ትናንት የጀመረው ብሔራዊ የሐዘን ቀኑ እስከ ነገ ድረስ የሚቆይ ይሆናል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ዐበይት_ጉዳዮች #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 411
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3716
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2493
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8286
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6771
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60646
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54583
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35143
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32732
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27828
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26962
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26479
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26140
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60646
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54583
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35143
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32732
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ተከፍሎ የማያልቅ የኢትዮጵያ እና ሕዝቧ ውለታ አለብን - የመናዊያን ፍልሰተኞች
Mar 19, 2026 2175
በዮሐንስ ደርበው ምድረ ቀደምቷ ሀገር ኢትዮጵያ ለተገፉ፣ ጥላ ከለላ ለሚሹ፣ ለተከዙና ለታረዙ የሀገራት ዜጎች መጠጊያ ናት። የኢትዮጵያን ቸርነትም ከተጠለሉባት እንግዶቿ በላይ ምሥክር የለም። የኢትዮጵያን ደጅ የረገጡ ሁሉ በቆይታቸው ለተደረገላቸው ሁሉ ‘ውለታችንን በምን እንክፈል’ ሲሉ ይደመጣሉ። ከአያሌ ሀገራት በመልከ ብዙ ቀውሶች ሳቢያ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሁሉ የቆሰሉ ልባቸው ታክሞ፣ ዕንባቸው ታብሶና ሕይወታቸው ታድሶ ኑራቸውን አደላድለዋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በዚህም ከአፍሪካም ሆነ ከተቀረው ክፍላተ ዓለም የጦርነትና ግጭት ጥላ ያጠላባቸውና ሰላምን የተጠሙ የቀጣናው ሀገራት ዜጎች ኢትዮጵያን ሲሹ ማየት የተለመደ ነው። የየመን ዜጎች ለዚህ ማሳያ ናቸው። ኢብቲሳም ኻሊድ እና መሰል የመናዊያን ከየመን የእርስ በርስ ግጭት በኋላ የኢትዮጵያን ደጅ ረግጠው ዛሬ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሚተርፍ የተድላ ኑሮ እየኖሩ ነው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረገችው ኢብቲሳም እንደምትለው፤ በየመን አለመረጋጋት በፈጠረው ጠባሳ እርሷና መሰሎቿ ለፍልሰት ተዳርገዋል። ለዚህ ደግሞ ምርጫቸው ኢትዮጵያ ሆነች። ወደ ኢትዮጵያም መጥተው የሀገሬው ፊት ሳይኮሰኩሳቸው በፍቅር እንደተቀበሏቸው ትናገራለች። በዚህም ዛሬ የመናዊያን ተስፋቸው ለምልሞ፣ ሕይወታቸው ሠምሮ ኢትዮጵያን እንደ እናት ቆጥረው እየኖሩ ስለመሆኑ ትናገራለች። ከ11 ዓመታት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የመጣችው ኢብቲሳም፤ በወቅቱ ቀኑ እንደጨለመባት ታወሳለች። ሰው ከቤቱ፣ ከወገኑ…ከሀገሩ ወጥቶ ወዴት ይሄዳል? በወቅቱ የነበረውን ጭንቀት ማየልም ታስታውሳለች። አሁን ግን ስለ ኢትዮጵያ እና ሕዝቧ በጎነት ዐውርታ አትጠግብም። “አሁን ፍልሰተኛ አይደለሁም፤ ያለሁት በሁለተኛዋ ሀገሬ ኢትዮጵያ ነውና” ትላለች። እንዲህ ባለው የረመዳን ወቅት ደግሞ የፍልሰተኞች ሁሉ ሰብሳቢ ናት። “ሁሉም ከእነ ቤተሰቡ ወደ ቤቷ እየመጣ ያፈጥራል። በዚህም በፍልሰት እንደመጡ ሳይሆን ቤተሰባዊነት ይሰማቸዋል። ከየመን፣ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ኤርትራ፣ አፍጋኒስታን፣ ኮንጎሊዝ (DRC) ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሁሉ ሰብሰብ ብለው የኢፍጣር መርሐ-ግብርን እንደሚያከናውኑም ታነሳለች። በዚህ ላይ ኢትዮጵያውያን ብርታት ናቸው ትላለች፤ ሁሌም ‘አይዟችሁ፣ በርቱ፣ ነገ ጥሩ ይሆናል’ እያሉ ያበረቱናል፤ ክብርና ፍቅር ይሰጡናል ስትልም ታስረዳለች። የኢትዮጵያንና ሕዝቧን ውለታ እንዴት መክፈል ይቻላል? ኢትዮጵያን ሀገራችን ብለን ነው እየጠራን ያለነው። እንደ እንግዳ እንደ ፍልሰተኛ እራሳችንን አናስብም፤ እንደሀገሬው አንዱ እንጅ፤ የምትለው ኢብቲሳም፤ ኢትዮጵያን እንዴት ብዬ ነው የምገልጻት? እናትን መግለጽ ይቻላል? እናትን መግለጽ ከተቻለ ኢትዮጵያን በዚያ ልክ መግለጽ ይቻል ይሆናል፤ እኔ ግን አይቻለኝም በማለት ትናገራለች። “የዛሬ 11 ዓመት ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት፤ የሰው ፊት አልገረፈኝም፤ ፊቱን ያዞረብኝም የለም። ኢትዮጵያውያን ደግ፣ ቅንና ደስ የምትሉ ሕዝቦች ናችሁ” ስትል ስሜቷን ትገልጻለች። ኢትዮጵያ እንደ ኒውዮርክ እያደገች ነው፤ እኛ ከመጣን በኋላ እንኳን በርካታ ለውጦች ዕያየን ነው ስትልም የኢትዮጵያን የለውጥ ሂደት አንስታለች። ለአብነትም ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በርካታ ነገሮች መስተካከላቸውን በመጠቆም፤ ለዚህም የኢትዮጵያን መንግሥት እናመሠግናለን ብላለች። ከፍልሰተኞች ጋር በተያያዘ በርካታ ሕጎች በመሻሻላቸው፤ ዛሬ በራሴ ስም ንግድ ፈቃድ አውጥቼ እየሠራሁ ነው፤ በጨረታዎችም እወዳደራለሁ፤ የበጎ አድራጎት ማኅበር መመሥረትና መምራት ችያለሁ። እነዚህ ሁሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ያመጣቸው ለውጦች ናቸው ብላለች። በምድረ ኢትዮጵያ ያለን ሁሉ ለኢትዮጵያ ዕድገት እንተባበር ስትልም ጥሪ አቅርባለች። ህልማችን ከኢትዮጵያውያን ጎን ሆነን ኢትዮጵያን በማሳደግ ጥረት በንቃት መሳተፍ ነው፤ የኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ውለታ መመለስ አለብን ስትልም ትናገራለች። በኢብቲሳም ኻሊድ ቤት በተዘጋጀ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይ የተሳተፈው አነስ አንዋር ለኢዜአ እንዳለው፤ ኢትዮጵያ በሯን ከፍታ አስጠልላዋለች። ከተለያዩ ሀገራት ብንመጣም ሰብሰብ ብለን ስናፈጥር፤ ማኅበራዊና ቤተሰባዊነታችን ይጠናክራል ብሏል። ብዙ ፈተናዎችን ዐይተናል፤ አልፈናቸው እዚህ ደርሰናል የሚለው አነስ፤ “ኢትዮጵያዊነት መልካምነት ነው” ሕዝቡ በክብር ነው የተቀበለን፤ ከምሥጋና ውጭ ምን ማለት እንችላለን? አመሥጋኞች ነን ሲል ገልጿል። እየተማርኩ ነው፤ ትምህርቴን አጠናቅቄ በሙያዬ በመሠማራት ኢትዮጵያን ማገዝ እፈልጋለሁ ብሏል። ራኪያ አሊ አብዱረዛቅ በበኩሏ በፈረንጆቹ 2011 ወደ ኢትዮጵያ መምጣቷን ታወሳለች። ትምህርቷንም ተከታትላ መመረቋን ገልጻ፤ ቤተሰብ አፍርታ ሁለት ልጆችንም ወልዳ እየኖረች ነው። ኢትዮጵያ ሁለተኛ ሀገሬ ናት፤ ሰላም አላት፤ ሕዝቡም ሰው አክባሪ ነው። ለኢትዮጵያ የተሻለ ልማት ደግሞ መተባበር ወሳኝ ስለሆነ ለዚሁ እንትጋ ስትል መልዕክቷን አስተላልፋለች። #ፍልሰተኞች #ኢዜአ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 605
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ።   እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል።   የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል።   በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል።   ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል።   በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም