ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በላሊበላ የገና በዓልን ከሃይማኖታዊ ስርአቱም ባለፈ የሰላም፣ የፍቅርና የመልካምነት መገለጫነቱን በሚያሳይ መልኩ አክብረናል- የበዓሉ ታዳሚዎች
Jan 8, 2026 5
ወልዲያ፤ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ )፡- በላሊበላ የገና በዓልን ከሃይማኖታዊ ስርአቱም ባለፈ የሰላም፣ የፍቅርና የመልካምነት መገለጫነቱን በሚያሳይ መልኩ አክብረናል ሲሉ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ታዳሚዎች ገለጹ። የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ገና በላሊበላ ከተማ በርካታ ምዕመናን፣ የውጭና የሀገር ውስጥ ታዳሚዎች በተገኙበት በላሊበላ ከተማ በድምቀት ተከብሯል። ከተለያዩ አካባቢዎች በክብረ በዓሉ ላይ ከተገኙት መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው ታዳሚዎች የገና በዓል አከባበር ከሃይማኖታዊ ክብረ በዓልነቱ ባለፈ የሰላም፣ የፍቅርና የመልካምነት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት በዓሉ በላሊበላ ከተማ በደማቅ ስነ ስርአት መከበሩን ገልጸው የአካባቢው ማህበረሰብ አቀባበልና መስተንግዶ የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። ከታዳሚዎቹ መካከል ወይዘሮ ተውባ አለባቸው በቆይታቸው ሃይማኖታዊ ስርአቱን ከማከናወንም ባለፈ ከብዙዎች ጋር ማህበራዊ ትስስርና አብሮነትን ያጠናከርንበት ነው ብለዋል። የላሊበላና አካባቢው ህብረተሰብ በጥሩ መስተንግዶ በመቀበል ፍቅርና አብሮነቱን በማሳየቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በኢትዮጵያ እነዚህንና መሰል የካበቱ የማህበረሰብና የባህል እሴቶችን በመጠበቅ የሀገር ሃብት አድርጎ መዝለቅ የጋራ ሃላፊነታችን ሊሆን ይገባል ብለዋል። ሌላኛው የበዓሉ ታዳሚ አቶ በየነ አለማው፤ በቆይታቸው መንፈሳዊ ዓላማቸውን ከማሳካትም ባለፈ ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመጡ እንግዶች ጋር ትውውቅ መፍጠራቸውን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ህዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላትን በአብሮነትና በመደጋገፍ የማክበር የቆየ እሴት መኖሩን አንስተው የሁሉም ነገር መሰረት የሆነውን ሰላምን በማጽናት ትብብርና አብሮነትን ይበልጥ ማጠንከር ይገባል ብለዋል። ከአዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ ላሊበላ ተገኝተው የገና በዓልን ያከበሩት ወይዘሮ አበበች ወልደማርያም፤ ድንቅ በሆነው ስፍራ ከውጭና ከሀገር ውስጥ ታዳሚዎች ጋር በማክበራቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። የሚያምርብንና ውበታችን አብሮነታቸን ነው ያሉት ወይዘሮ አበበች የሀገራችንን ሰላም በማረጋገጥ እምቅ የሆኑ ሃብቶችን በመጠበቅ ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባናል ብለዋል። በቆይታቸው የላሊበላ ከተማና አካባቢው ህዝብ ላደረገላቸው መልካም አቀባበል እና እንክብካቤ አመስግነዋል።
በኦሮሚያ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁለንተናዊ ልማትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jan 8, 2026 33
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁለንተናዊ ልማትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ገለጹ። በክልሉ እስካሁን ከ22ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውን አስታውሰው ሰላምን በመግፋት በጥፋታቸው በቀጠሉት ላይ ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ፤ የክልሉን ወቅታዊ የሰላምና የልማት እንቅስቃሴ በማስመልከት ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የክልሉ መንግስት ከለውጡ ወዲህ ከገጠሙት ፈተናዎች መካከል በተወሰኑ አካባቢዎች የጸጥታ ችግር እንደነበር አስታውሰው በዘላቂነት ለመፍታት ብዙ መሰራቱን አስረድተዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን ከማስከበር በተጓዳኝ የተሳሳተ መንገድ ላይ የነበሩ አካላት ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ጥረት ተደርጓል ብለዋል። ከመንግስት የሰላም ጥሪ ባለፈ በአባ ገዳዎች፣ በሃዳ ሲንቄዎች፣ በሃይማኖት አባቶች እና በሀገር ሽማግሌዎች አማካኝነት ለሰላም ምላሽ እንዲሰጡ መሰራቱን አንስተዋል። በዚህም መሰረት ከ22 ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪን በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ሰላማዊ ህይወት መመለሳቸውን ገልጸዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል 10ሺህ የሚሆኑት የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ሲሆን ሌሎች እንደየፍላጎታቸው ወደ መደበኛ ህይወታቸው ተመልሰዋል ብለዋል። የመስሪያ ቦታ እና 581 ሚሊዮን ብር ብድር ተመቻችቶላቸው ወደ ስራ የገቡ እንዳሉ ገልጸው ወደ ትምህርት እና ወደ መንግስት ስራም የተመለሱ እንዳሉ ጠቅሰዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁለንተናዊ ልማትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል። “በጽንፈኝነት ለጥፋት ዓላማ የተሰለፈ ሁሉ የትኛውንም ቋንቋ ቢናገር ጽንፈኛ ነው” ያሉት አቶ ሃይሉ የኦሮሞም ይሁን የአማራ ጽንፈኛ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ይጠናከራል ብለዋል። በቅርቡ በሆሮ ጉዱሩ እና ምስራቅ ወለጋ ዞኖች የተወሰኑ አካባቢዎች በጽንፈኞች ላይ ጠንካራ እርምጃ በመወሰዱ በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።
በጅማ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የቱሪዝም ልማት ሥራዎች ለዘርፉ ዕድገት ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ ነው
Jan 8, 2026 50
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የቱሪዝም መስህብ ልማት ሥራዎች ምቹ የመዳረሻ ምህዳር እየፈጠሩ መሆናቸውን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ገለጸ። ጅማ ዞን በሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ ሀብት እምቅ አቅም ያለው ሲሆን በኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ጅማ ከፍተኛ ጥራት ያለው የቡና ምርት ከሚገኝባቸው ቀጠናዎች አንዱ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የቡና ማሳዎችንና የዝግጅት ሂደቶችን ለጎብኚዎች ክፍት በማድረግ የቡና ቱሪዝምን ለማሳደግ እየተሠራ ይገኛል። በዞኑ የሚገኘው የደን ሽፋን ለአካባቢ ተስማሚ ቱሪዝም ወይንም ኢኮ-ቱሪዝም ትልቅ ዕድል ያለው ነው፡፡ የጅማ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ኒሜሪ አባተማም ለኢዜአ እንደገለጹት፤ እያንዳንዱ ወረዳ ቢያንስ አንድ የቱሪስት መዳረሻ እንዲኖረው ሰፋፊ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ እስካሁንም በ21 አዳዲስ ግንባታ ከተጀመረባቸው ወረዳዎች መካከል የሦስቱ ተጠናቀው ለተጠቃሚ ክፍት መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ እነኚህም ነዲ ጊቤ፣ ሊሙ ኮሳ እና ሊሙ ገነት ወረዳዎች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በሌሎቹም ቦታ የመለየት፣ በጀት የመያዝ እንዲሁም የማልማት ስራዎች መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡ በዞኑ የሚገኙ እምቅ የቱሪዝም መስህቦችን ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች በማስተዋወቅ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡ የቱሪስት ፍሰቱን ለመጨመርና የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም መሠረተ ልማት ወሳኝ በመሆኑም በጅማ ከተማ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች እንዲገነቡ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በዞኑ በሚገኙ ቀበሌዎች የመንገድ መሠረተ ልማት የማሟላት ሥራ መከናወኑን ጠቁመው፤ የመዳረሻ ልማቱ ከኮሪደር ልማት ጋር በመሰናሰል እስከ አርሶ አደር ቀዬ እንዲደርስ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ እነዚህ የልማት ሥራዎች የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው፤ ዘርፉን በዘላቂነት ለማሳደግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሠሩ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ ይህም ዞኑን ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ በማድረግ የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ጠቁመዋል።
ነጌሌ አርሲ ተከታታይ አራተኛ ድሉን አስመዘገበ
Jan 8, 2026 46
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ነጌሌ አርሲ ምድረ ገነት ሽሬን 1 ለ 0 አሸንፏል። የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ይጫወታል አሁናዊ ቁጥራዊ መረጃዎች ስለ 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ከቤ ብዙነህ በ12ኛው ደቂቃ ላይ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ነጌሌ አርሲ በ25 ነጥብ ደረጃውን ከሶስተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ምድረ ገነት ሽሬ በ17 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። የማድሪድ ደርቢ በስፔን አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል እና ሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
ኢትዮጵያ እና ቻይና በዘርፈ-ብዙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ ለማጠናከር ተወያዩ
Jan 8, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ በርካታ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ አጠናክረው ማስቀጠል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ተቀብዬ በጽናት በሚጓዘው የኢትዮጵያ እና ቻይና የመንግሥት እና ሕዝብ ግንኙነት ላይ ተነጋግረናል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ ኢትዮጵያ እና ቻይና ለአስርት ዓመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። ይኽ ግንኙነት በቅርቡ ወደ በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የስትራቴጂክ ትብብር ማደጉንም አስታውቀዋል። በተለያዩ የልማት ትብብር ርዕሰ ጉዳዮችን ለማከናወን ያለንን ጽኑ አቋም በማስቀጠል ላይ ውይይት አድርገናልም ነው ያሉት። በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ እና ቻይና በዘርፈ-ብዙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ ለማጠናከር ተወያዩ
Jan 8, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ በርካታ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ አጠናክረው ማስቀጠል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ተቀብዬ በጽናት በሚጓዘው የኢትዮጵያ እና ቻይና የመንግሥት እና ሕዝብ ግንኙነት ላይ ተነጋግረናል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ ኢትዮጵያ እና ቻይና ለአስርት ዓመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። ይኽ ግንኙነት በቅርቡ ወደ በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የስትራቴጂክ ትብብር ማደጉንም አስታውቀዋል። በተለያዩ የልማት ትብብር ርዕሰ ጉዳዮችን ለማከናወን ያለንን ጽኑ አቋም በማስቀጠል ላይ ውይይት አድርገናልም ነው ያሉት። በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ
Jan 8, 2026 76
አዲስ አበባ ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ዛሬ መቀበላቸውንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። ጉብኝቱ የወል ፍላጎት በሆኑ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን ያካትታል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክቷል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
Jan 6, 2026 298
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም መሰረት፦ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የማዳበሪያ ምርት ፈቃድ እና የፖታሽ ማዕድን ምርት ፈቃድ ረቂቅ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ለምክር ቤቱ የቀረቡት ሁለት ረቂቅ ስምምነቶች የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር፣ ሀገራችን ለማዳበሪያ ግዥ የምታወጣውን ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ ለማስቀረት እና ለሀገራችን አርሶ አደሮች ወቅቱን የጠበቀ የማዳበሪያ ስርጭት እንዲኖር ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውና ከአካባቢ ጥበቃና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት አንጻርም የመንግስትን የፖሊሲ አቅጣጫ የተከተሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ የማዕድን ሚኒስቴር ስምምነቶቹን እንዲፈራረምና ወደ ስራ እንዲገቡ ምክርቤቱ በሙሉ ድምጽ ይሁንታ ሰጥቷል፡፡ 2. በመቀጠል የቤት ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ምከር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ ባለፉት አመታት በቂ የቤት አቅርቦት እንዲኖር የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም አሁንም የቤት አቅርቦትና ፍላጎት የተጣጣመ አይደለም፡፡ በመሆኑም በከተማና በገጠርለሚኖሩ ለሁሉም ዜጎች አቅምን ያገናዘበ፣ ተደራሽ እና በቂ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችል የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው ከኮሪያ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ ጋር በተደረገው የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት ላይ ነው፡፡ የብድር ስምምነቱ ለህከምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፕሮጄክት ምዕራፍ 2 ማስፈፀሚያ የሚውል 30,000,000 /ሰላሳ ሚሊዮን/የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኝ ሲሆን የሀከምና መሳሪያዎችን ችግር የሚፈታ፣ ዝቅተኛ ወለድ 0.01% የሚከፈልበት እና የከ5 አመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምከር ቤቱም ብድሩ ከሀገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋርየሚጣጣም መሆኑን በማረጋገጥ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው የተለያዩ አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ከፍያን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ተቋሙ ለተገልጋዮች ጥራትና ተዓማኒነት ያላቸው አገልግሎቶች ለመስጠት የሚያወጣቸውን ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ ወጪዎች የአገልግሎቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ ከሆነው የህብረተሰብ ክፍል ተመጣጣኝ ከፍያ በማስከፈል እንዲሸፍን ለማድረግ እንዲያስችለው ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምከር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይበሰፊው ከተወያየበት በኋላ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ደምጽ ወስኗል፡፡ 5. እንዲሁም የኅብረት ሥራ ማህበራት ማሻሻያ አዋጅ ምክር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 985/2009 ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ከተቀመጡ አቅጣጫዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማድረግ አዋጁን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 6. በማስከተልም የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቷል፡፡በአየር ትራንስፖርት ደህንነት፡ አስተማማኝነትና ቅልጥፍና ላይ የሚስተዋሉ የደህንነት ስጋቶችን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል አሰራር ለመተግበርየአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅ ቁጥር 432/1997ን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 7. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት ደንቦች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው የመሶብ አገልግሎትን ለማቋቋም የወጣው ደንብ ተገልጋዮች የመንግስት አገልግሎት ለማግኘት የሚያባከኑትን ጊዜ፣ ወጭ እና ጉልበት በመቆጠብ የተገልጋይ እርካታን የሚጨምርየአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ለመተግበር እንዲያስችል የቀረበ ሲሆን ሁለተኛው የኢትዮጵያ የብቃትና ሥራ አመራርኢንስቲትዩት አደረጃጀት፣ ሥልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣው ደንብ ተቋሙ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባርና ሃላፊነት ለመወጣት እንዲያስችለው ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ምክር ቤቱም በሁለቱም ደንቦች ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 8. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው የሁሉን አቀፍ የተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠን፣ ምንጭ እና አስተዳደርን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ደንቡ በኢትዮጵያ የኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 148/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ (3) መሰረት የተቋቋመው የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሁሉን አቀፍ ተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠንና ምንጭ እንዲሁም ፈንዱ ስለሚተዳደርበት ሁኔታ ለመወሰን ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 9. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲዊ ሪፐብሊክ የስፖርት ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የስፖርት ፖሊሲ የማህበረሰቡን የስፖርት ተሳትፎ ከማረጋገጥ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርአት ከመዘርጋት፣ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋት የአበረታች ቅመሞችና ዘዴዎች ከመከላከል እና ስፖርትን ለማህበራዊ ልማት ከመጠቀም አንጻር ከፍተቶች የነበሩበት በመሆኑ ፖሊሲውን ለማሻሻል ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 10. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የስፖርት ዘርፍ ካለው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲሁም አስተዳደራዊ ውስብስብነት አንጻር ዘርፉን በአግባቡ ለመምራት ዘመናዊ፣ አሳታፊና አካታች የሆነ የህግ ማዕቀፍና አስተዳደራዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርን ሹመት አጸደቀ
Jan 6, 2026 220
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርን ሹመት አጽድቋል። ምክር ቤቱ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ አካሂዷል። በዚህም ምክር ቤቱ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ወይዘሮ ሃይማኖት ዘለቀ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ የቀረበውን ረቂቅ መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡ ወይዘሮ ኃይማኖት ዘለቀ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሪፖርተርነት እስከ አርታኢነት እንዲሁም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በሙያቸው አገልግለዋል፡፡ በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽህፈት ቤት በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሀላፊ በመሆን ማገልገላቸው ተገልጿል፡፡ እንዲሁም በቀድሞ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት በመስራት ሀገራቸውን አገልግለዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክር፣ የዲሞክራሲ ባህልና የተቋማት ግንባታ ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ናቸው
Jan 6, 2026 155
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ምክክር፣ የዲሞክራሲ ባህልና የተቋማት ግንባታ ሥራዎች ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ወሳኝ መሰረት መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያን ችግሮች በመፍታት በተደመረ አቅም ሀገርን ለማበልፀግ ምሁራን ሀሳብ ከማመንጨትና ችግር ፈች ጥናት ከማድረግ ጀምሮ በተግባር ለውጥ የሚያመጣ ሥራን ሊከውኑ እንደሚገባም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን በማስመልከት “የምሁራን ሚና ለሀገር ብልፅግና” በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፖለቲካ ልዩነቶችን እንዴት ነው መፍታት የሚቻለው በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፥ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ልዩነቶችን መፍታት የቁርጠኝነትና የአቋም ጉዳይ መሆን አለበት ብለዋል። በየአካባቢው ያሉ የጽንፍ እሳቤዎች ኢትዮጵያን አንድ እርምጃ ወደ ፊት እንደማይወስዱ በማንሳት፥ ኢትዮጵያ የጋራችን ናት በሚል እሳቤ አምነን ከሠራን ወደተሻለ ምዕራፍ እንሻገራለን ነው ያሉት። ታሪክን በሚዛን፣ ዛሬን በትጋት፣ ነገን በተስፋ ነው የምንመለከተው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለሁሉም ህብረተሰብ እኩል እድል መስጠት እንደሚገባ ጠቅሰዋል። ጠንካራ ሀገራዊ አንድነት መፍጠር የሚቻለው የወል ትርክት በመገንባት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አንስተዋል።
የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለናል - የቀድሞ ታጣቂዎች
Jan 5, 2026 268
ጎንደር፤ ታህሳስ 27/2018(ኢዜአ)፦ የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለናል ሲሉ በአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በክልሉ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን ጥሪ በመቀበል የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን ለመንግስት በማስረከብ በጠዳ የስልጠና ማእከል የተሀድሶ ስልጠና ጀምረዋል። በስልጠና ላይ ካሉት የቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው አስቻለው እሸቴ፣ አስቻለው ዳርጌ እና አንዳርጌ ሲሳይ፤ የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን መጥተናል ብለዋል። በክልሉ የውክልና ጦርነት ተልእኮ ፈፃሚ በመሆን ሰላምን ማናጋትና ህዝብን መጉዳት ታጋይነት ሳይሆን ባንዳነት መሆኑን ያነሱት ሰልጣኞቹ የነበርንበት መንገድ ፍፁም ስህተት መሆኑን ተገንዝበናል ሲሉ ተናግረዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል አስቻለው እሸቴ፤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን ከጥፋት መንገድ ወጥተን መጥተናል፤ የበደልነውን ህዝብም በልማት ለመካስ ተዘጋጅተናል ብሏል። በክልሉ የተሳሳተ መንገድ ላይ የነበሩ ወጣቶች እየተመለሱ መሆኑን አንስቶ እርሱና ጓደኞቹም ይህንኑ እድል በመጠቀም መምጣታቸውን ተናግሯል። በመሆኑም ሌሎችም ጊዜ ሳያባክኑ ትጥቃቸውን በማስረከብ ለሰላማዊ ህይወት ተዘጋጅተው እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። ሌላኛው የቀድሞ ታጣቂ አስቻለው ዳርጌ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ሰርቶ ለመለወጥና የሰላም አምባሳደር በመሆን ህዝብን ለማገልገል መምጣቱን ተናግሯል። የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የጥፋት መሳሪያ መሆን ከባንዳነት ውጭ ሌላ ትርጉም የሌለው መሆኑን አንስቶ፤ በጥፋቱ በመፀፀት ህዝብን በልማት ለመካስ መምጣቱን ገልጿል። በመሆኑም የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ስልጠናውን ወስዶ ወደ ነበረበት ሰላማዊ ህይወት በመመለስ የበደለውን ህዝብ በልማት ለመካስ መዘጋጀቱን ገልጿል። የአማራ ክልል ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሃላፊ በሪሁን መንግስቴ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በየእለቱ እየመጡ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም የቀድሞ ታጣቂዎቹን በመቀበልና የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት መልሰው እንዲቋቋሙ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ እየመጣ ላለው ሰላም የመንግስት ቁርጠኝነት እንዳለ ሆኖ በተለይም የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አጠቃላይ የህዝቡ ድምር ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።
የምርጫ ሂደት በቴክኖሎጂ መታገዝ ሂደቱን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተዓማኒ ያደርገዋል
Jan 5, 2026 284
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 27/2018(ኢዜአ)፦ የምርጫ ሂደት በቴክኖሎጂ የታገዘ መሆን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተዓማኒ ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንዳለው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ30 ሺህ በላይ በሚሆኑ የምርጫ ክልሎች የእጩዎችና የመራጮች ምዝገባ በዲጂታል እንደሚከናወን አስታውቋል። ቦርዱ ዲጂታል የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ ሥርዓትን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ወቅት፥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫን በገለልተኝነትና በታማኝነት ለማስፈጸም መቋቋሙን አንስተዋል። በዚህ ረገድ ቦርዱ 7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛና ፍትሐዊ ለማድረግ አሰራሩን በቴክኖሎጂ እየደገፈ ነው ብለዋል። የምርጫ ሂደትን በቴክኖሎጂ መደገፍ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፥ ሂደቱን ግልጽና ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ ጉልህ ሚና እንዳለው አንስተዋል። ቴክኖሎጂ ምርጫን ለማሳለጥ ያለው ሚና የጎላ መሆኑን ጠቅሰው፤ ስለቴክኖሎጂው አጠቃቀም በቂ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባ ተናግረዋል። ቦርዱ የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባን በዲጂታል መደገፉ ከወረቀት አሰራር እየወጣ መሆኑን የሚያመላክት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ በበኩላቸው ቦርዱ በአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅዱ ውስጥ ካካተታቸው ጉዳዮች አንዱ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር ነው ብለዋል። በዚህም 7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ በቴክኖሎጂ ለመደገፍ ሁለት ሶፍትዌሮች መልማታቸውን ነው የተናገሩት። የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባ በቴክኖሎጂ መታገዙ ጊዜና ገንዘብ ከመቆጠብ ባለፈ ዴሞክራሲያዊ መብትን በአግባቡ ለመጠቀምና የመረጃ አያያዝ ችግርን ለመፍታት ያስችላል ብለዋል። የቦርዱን አሰራር ቀልጣፋና ዘመናዊ ከማድረግ አኳያ ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው ዕጩዎችና መራጮች ባሉበት ሆነው መመዝገብ የሚችሉበት ነው ብለዋል። ከ55 ሺህ የምርጫ ክልሎች መካከል ከ30 ሺህ በላይ በሚሆኑት የእጩዎችና የመራጮች ምዝገባ በዲጂታል እንደሚከናወንም ገልጸዋል። በዲጂታል መመዝገብ ላልቻሉ መራጮችና ዕጩዎች በወረቀት የሚመዘገቡበት አሰራር መኖሩንም ነው ሰብሳቢዋ የተናገሩት። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ፣ የዴሞክራሲ ተቋማት እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ታድመዋል። ቦርዱ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ እና ቻይና በዘርፈ-ብዙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ ለማጠናከር ተወያዩ
Jan 8, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ በርካታ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ አጠናክረው ማስቀጠል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ተቀብዬ በጽናት በሚጓዘው የኢትዮጵያ እና ቻይና የመንግሥት እና ሕዝብ ግንኙነት ላይ ተነጋግረናል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ ኢትዮጵያ እና ቻይና ለአስርት ዓመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። ይኽ ግንኙነት በቅርቡ ወደ በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የስትራቴጂክ ትብብር ማደጉንም አስታውቀዋል። በተለያዩ የልማት ትብብር ርዕሰ ጉዳዮችን ለማከናወን ያለንን ጽኑ አቋም በማስቀጠል ላይ ውይይት አድርገናልም ነው ያሉት። በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ
Jan 8, 2026 76
አዲስ አበባ ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ዛሬ መቀበላቸውንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። ጉብኝቱ የወል ፍላጎት በሆኑ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ የሚደረጉ ውይይቶችን ያካትታል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክቷል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
Jan 6, 2026 298
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም መሰረት፦ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የማዳበሪያ ምርት ፈቃድ እና የፖታሽ ማዕድን ምርት ፈቃድ ረቂቅ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ለምክር ቤቱ የቀረቡት ሁለት ረቂቅ ስምምነቶች የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር፣ ሀገራችን ለማዳበሪያ ግዥ የምታወጣውን ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ ለማስቀረት እና ለሀገራችን አርሶ አደሮች ወቅቱን የጠበቀ የማዳበሪያ ስርጭት እንዲኖር ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውና ከአካባቢ ጥበቃና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት አንጻርም የመንግስትን የፖሊሲ አቅጣጫ የተከተሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ የማዕድን ሚኒስቴር ስምምነቶቹን እንዲፈራረምና ወደ ስራ እንዲገቡ ምክርቤቱ በሙሉ ድምጽ ይሁንታ ሰጥቷል፡፡ 2. በመቀጠል የቤት ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ምከር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ ባለፉት አመታት በቂ የቤት አቅርቦት እንዲኖር የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም አሁንም የቤት አቅርቦትና ፍላጎት የተጣጣመ አይደለም፡፡ በመሆኑም በከተማና በገጠርለሚኖሩ ለሁሉም ዜጎች አቅምን ያገናዘበ፣ ተደራሽ እና በቂ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችል የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው ከኮሪያ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ ጋር በተደረገው የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት ላይ ነው፡፡ የብድር ስምምነቱ ለህከምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፕሮጄክት ምዕራፍ 2 ማስፈፀሚያ የሚውል 30,000,000 /ሰላሳ ሚሊዮን/የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኝ ሲሆን የሀከምና መሳሪያዎችን ችግር የሚፈታ፣ ዝቅተኛ ወለድ 0.01% የሚከፈልበት እና የከ5 አመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምከር ቤቱም ብድሩ ከሀገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋርየሚጣጣም መሆኑን በማረጋገጥ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው የተለያዩ አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ከፍያን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ተቋሙ ለተገልጋዮች ጥራትና ተዓማኒነት ያላቸው አገልግሎቶች ለመስጠት የሚያወጣቸውን ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ ወጪዎች የአገልግሎቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ ከሆነው የህብረተሰብ ክፍል ተመጣጣኝ ከፍያ በማስከፈል እንዲሸፍን ለማድረግ እንዲያስችለው ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምከር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይበሰፊው ከተወያየበት በኋላ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ደምጽ ወስኗል፡፡ 5. እንዲሁም የኅብረት ሥራ ማህበራት ማሻሻያ አዋጅ ምክር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 985/2009 ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ከተቀመጡ አቅጣጫዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማድረግ አዋጁን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 6. በማስከተልም የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቷል፡፡በአየር ትራንስፖርት ደህንነት፡ አስተማማኝነትና ቅልጥፍና ላይ የሚስተዋሉ የደህንነት ስጋቶችን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል አሰራር ለመተግበርየአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅ ቁጥር 432/1997ን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 7. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት ደንቦች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው የመሶብ አገልግሎትን ለማቋቋም የወጣው ደንብ ተገልጋዮች የመንግስት አገልግሎት ለማግኘት የሚያባከኑትን ጊዜ፣ ወጭ እና ጉልበት በመቆጠብ የተገልጋይ እርካታን የሚጨምርየአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ለመተግበር እንዲያስችል የቀረበ ሲሆን ሁለተኛው የኢትዮጵያ የብቃትና ሥራ አመራርኢንስቲትዩት አደረጃጀት፣ ሥልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣው ደንብ ተቋሙ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባርና ሃላፊነት ለመወጣት እንዲያስችለው ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ምክር ቤቱም በሁለቱም ደንቦች ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 8. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው የሁሉን አቀፍ የተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠን፣ ምንጭ እና አስተዳደርን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ደንቡ በኢትዮጵያ የኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 148/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ (3) መሰረት የተቋቋመው የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሁሉን አቀፍ ተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠንና ምንጭ እንዲሁም ፈንዱ ስለሚተዳደርበት ሁኔታ ለመወሰን ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 9. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲዊ ሪፐብሊክ የስፖርት ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የስፖርት ፖሊሲ የማህበረሰቡን የስፖርት ተሳትፎ ከማረጋገጥ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርአት ከመዘርጋት፣ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋት የአበረታች ቅመሞችና ዘዴዎች ከመከላከል እና ስፖርትን ለማህበራዊ ልማት ከመጠቀም አንጻር ከፍተቶች የነበሩበት በመሆኑ ፖሊሲውን ለማሻሻል ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 10. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የስፖርት ዘርፍ ካለው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲሁም አስተዳደራዊ ውስብስብነት አንጻር ዘርፉን በአግባቡ ለመምራት ዘመናዊ፣ አሳታፊና አካታች የሆነ የህግ ማዕቀፍና አስተዳደራዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርን ሹመት አጸደቀ
Jan 6, 2026 220
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርን ሹመት አጽድቋል። ምክር ቤቱ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ አካሂዷል። በዚህም ምክር ቤቱ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ወይዘሮ ሃይማኖት ዘለቀ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ የቀረበውን ረቂቅ መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡ ወይዘሮ ኃይማኖት ዘለቀ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሪፖርተርነት እስከ አርታኢነት እንዲሁም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በሙያቸው አገልግለዋል፡፡ በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽህፈት ቤት በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሀላፊ በመሆን ማገልገላቸው ተገልጿል፡፡ እንዲሁም በቀድሞ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት በመስራት ሀገራቸውን አገልግለዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክር፣ የዲሞክራሲ ባህልና የተቋማት ግንባታ ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ናቸው
Jan 6, 2026 155
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ምክክር፣ የዲሞክራሲ ባህልና የተቋማት ግንባታ ሥራዎች ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ወሳኝ መሰረት መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያን ችግሮች በመፍታት በተደመረ አቅም ሀገርን ለማበልፀግ ምሁራን ሀሳብ ከማመንጨትና ችግር ፈች ጥናት ከማድረግ ጀምሮ በተግባር ለውጥ የሚያመጣ ሥራን ሊከውኑ እንደሚገባም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን በማስመልከት “የምሁራን ሚና ለሀገር ብልፅግና” በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፖለቲካ ልዩነቶችን እንዴት ነው መፍታት የሚቻለው በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፥ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ልዩነቶችን መፍታት የቁርጠኝነትና የአቋም ጉዳይ መሆን አለበት ብለዋል። በየአካባቢው ያሉ የጽንፍ እሳቤዎች ኢትዮጵያን አንድ እርምጃ ወደ ፊት እንደማይወስዱ በማንሳት፥ ኢትዮጵያ የጋራችን ናት በሚል እሳቤ አምነን ከሠራን ወደተሻለ ምዕራፍ እንሻገራለን ነው ያሉት። ታሪክን በሚዛን፣ ዛሬን በትጋት፣ ነገን በተስፋ ነው የምንመለከተው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለሁሉም ህብረተሰብ እኩል እድል መስጠት እንደሚገባ ጠቅሰዋል። ጠንካራ ሀገራዊ አንድነት መፍጠር የሚቻለው የወል ትርክት በመገንባት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አንስተዋል።
የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለናል - የቀድሞ ታጣቂዎች
Jan 5, 2026 268
ጎንደር፤ ታህሳስ 27/2018(ኢዜአ)፦ የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለናል ሲሉ በአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በክልሉ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን ጥሪ በመቀበል የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን ለመንግስት በማስረከብ በጠዳ የስልጠና ማእከል የተሀድሶ ስልጠና ጀምረዋል። በስልጠና ላይ ካሉት የቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው አስቻለው እሸቴ፣ አስቻለው ዳርጌ እና አንዳርጌ ሲሳይ፤ የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን መጥተናል ብለዋል። በክልሉ የውክልና ጦርነት ተልእኮ ፈፃሚ በመሆን ሰላምን ማናጋትና ህዝብን መጉዳት ታጋይነት ሳይሆን ባንዳነት መሆኑን ያነሱት ሰልጣኞቹ የነበርንበት መንገድ ፍፁም ስህተት መሆኑን ተገንዝበናል ሲሉ ተናግረዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል አስቻለው እሸቴ፤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን ከጥፋት መንገድ ወጥተን መጥተናል፤ የበደልነውን ህዝብም በልማት ለመካስ ተዘጋጅተናል ብሏል። በክልሉ የተሳሳተ መንገድ ላይ የነበሩ ወጣቶች እየተመለሱ መሆኑን አንስቶ እርሱና ጓደኞቹም ይህንኑ እድል በመጠቀም መምጣታቸውን ተናግሯል። በመሆኑም ሌሎችም ጊዜ ሳያባክኑ ትጥቃቸውን በማስረከብ ለሰላማዊ ህይወት ተዘጋጅተው እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። ሌላኛው የቀድሞ ታጣቂ አስቻለው ዳርጌ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ሰርቶ ለመለወጥና የሰላም አምባሳደር በመሆን ህዝብን ለማገልገል መምጣቱን ተናግሯል። የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የጥፋት መሳሪያ መሆን ከባንዳነት ውጭ ሌላ ትርጉም የሌለው መሆኑን አንስቶ፤ በጥፋቱ በመፀፀት ህዝብን በልማት ለመካስ መምጣቱን ገልጿል። በመሆኑም የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ስልጠናውን ወስዶ ወደ ነበረበት ሰላማዊ ህይወት በመመለስ የበደለውን ህዝብ በልማት ለመካስ መዘጋጀቱን ገልጿል። የአማራ ክልል ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሃላፊ በሪሁን መንግስቴ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በየእለቱ እየመጡ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም የቀድሞ ታጣቂዎቹን በመቀበልና የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት መልሰው እንዲቋቋሙ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ እየመጣ ላለው ሰላም የመንግስት ቁርጠኝነት እንዳለ ሆኖ በተለይም የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አጠቃላይ የህዝቡ ድምር ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።
የምርጫ ሂደት በቴክኖሎጂ መታገዝ ሂደቱን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተዓማኒ ያደርገዋል
Jan 5, 2026 284
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 27/2018(ኢዜአ)፦ የምርጫ ሂደት በቴክኖሎጂ የታገዘ መሆን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተዓማኒ ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንዳለው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ30 ሺህ በላይ በሚሆኑ የምርጫ ክልሎች የእጩዎችና የመራጮች ምዝገባ በዲጂታል እንደሚከናወን አስታውቋል። ቦርዱ ዲጂታል የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ ሥርዓትን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ወቅት፥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫን በገለልተኝነትና በታማኝነት ለማስፈጸም መቋቋሙን አንስተዋል። በዚህ ረገድ ቦርዱ 7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛና ፍትሐዊ ለማድረግ አሰራሩን በቴክኖሎጂ እየደገፈ ነው ብለዋል። የምርጫ ሂደትን በቴክኖሎጂ መደገፍ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፥ ሂደቱን ግልጽና ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ ጉልህ ሚና እንዳለው አንስተዋል። ቴክኖሎጂ ምርጫን ለማሳለጥ ያለው ሚና የጎላ መሆኑን ጠቅሰው፤ ስለቴክኖሎጂው አጠቃቀም በቂ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባ ተናግረዋል። ቦርዱ የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባን በዲጂታል መደገፉ ከወረቀት አሰራር እየወጣ መሆኑን የሚያመላክት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ በበኩላቸው ቦርዱ በአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅዱ ውስጥ ካካተታቸው ጉዳዮች አንዱ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር ነው ብለዋል። በዚህም 7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ በቴክኖሎጂ ለመደገፍ ሁለት ሶፍትዌሮች መልማታቸውን ነው የተናገሩት። የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባ በቴክኖሎጂ መታገዙ ጊዜና ገንዘብ ከመቆጠብ ባለፈ ዴሞክራሲያዊ መብትን በአግባቡ ለመጠቀምና የመረጃ አያያዝ ችግርን ለመፍታት ያስችላል ብለዋል። የቦርዱን አሰራር ቀልጣፋና ዘመናዊ ከማድረግ አኳያ ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው ዕጩዎችና መራጮች ባሉበት ሆነው መመዝገብ የሚችሉበት ነው ብለዋል። ከ55 ሺህ የምርጫ ክልሎች መካከል ከ30 ሺህ በላይ በሚሆኑት የእጩዎችና የመራጮች ምዝገባ በዲጂታል እንደሚከናወንም ገልጸዋል። በዲጂታል መመዝገብ ላልቻሉ መራጮችና ዕጩዎች በወረቀት የሚመዘገቡበት አሰራር መኖሩንም ነው ሰብሳቢዋ የተናገሩት። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቱ አለነ፣ የዴሞክራሲ ተቋማት እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ታድመዋል። ቦርዱ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።
ማህበራዊ
በላሊበላ የገና በዓልን ከሃይማኖታዊ ስርአቱም ባለፈ የሰላም፣ የፍቅርና የመልካምነት መገለጫነቱን በሚያሳይ መልኩ አክብረናል- የበዓሉ ታዳሚዎች
Jan 8, 2026 5
ወልዲያ፤ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ )፡- በላሊበላ የገና በዓልን ከሃይማኖታዊ ስርአቱም ባለፈ የሰላም፣ የፍቅርና የመልካምነት መገለጫነቱን በሚያሳይ መልኩ አክብረናል ሲሉ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ታዳሚዎች ገለጹ። የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ገና በላሊበላ ከተማ በርካታ ምዕመናን፣ የውጭና የሀገር ውስጥ ታዳሚዎች በተገኙበት በላሊበላ ከተማ በድምቀት ተከብሯል። ከተለያዩ አካባቢዎች በክብረ በዓሉ ላይ ከተገኙት መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው ታዳሚዎች የገና በዓል አከባበር ከሃይማኖታዊ ክብረ በዓልነቱ ባለፈ የሰላም፣ የፍቅርና የመልካምነት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት በዓሉ በላሊበላ ከተማ በደማቅ ስነ ስርአት መከበሩን ገልጸው የአካባቢው ማህበረሰብ አቀባበልና መስተንግዶ የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። ከታዳሚዎቹ መካከል ወይዘሮ ተውባ አለባቸው በቆይታቸው ሃይማኖታዊ ስርአቱን ከማከናወንም ባለፈ ከብዙዎች ጋር ማህበራዊ ትስስርና አብሮነትን ያጠናከርንበት ነው ብለዋል። የላሊበላና አካባቢው ህብረተሰብ በጥሩ መስተንግዶ በመቀበል ፍቅርና አብሮነቱን በማሳየቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በኢትዮጵያ እነዚህንና መሰል የካበቱ የማህበረሰብና የባህል እሴቶችን በመጠበቅ የሀገር ሃብት አድርጎ መዝለቅ የጋራ ሃላፊነታችን ሊሆን ይገባል ብለዋል። ሌላኛው የበዓሉ ታዳሚ አቶ በየነ አለማው፤ በቆይታቸው መንፈሳዊ ዓላማቸውን ከማሳካትም ባለፈ ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመጡ እንግዶች ጋር ትውውቅ መፍጠራቸውን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ህዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላትን በአብሮነትና በመደጋገፍ የማክበር የቆየ እሴት መኖሩን አንስተው የሁሉም ነገር መሰረት የሆነውን ሰላምን በማጽናት ትብብርና አብሮነትን ይበልጥ ማጠንከር ይገባል ብለዋል። ከአዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ ላሊበላ ተገኝተው የገና በዓልን ያከበሩት ወይዘሮ አበበች ወልደማርያም፤ ድንቅ በሆነው ስፍራ ከውጭና ከሀገር ውስጥ ታዳሚዎች ጋር በማክበራቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። የሚያምርብንና ውበታችን አብሮነታቸን ነው ያሉት ወይዘሮ አበበች የሀገራችንን ሰላም በማረጋገጥ እምቅ የሆኑ ሃብቶችን በመጠበቅ ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባናል ብለዋል። በቆይታቸው የላሊበላ ከተማና አካባቢው ህዝብ ላደረገላቸው መልካም አቀባበል እና እንክብካቤ አመስግነዋል።
በጅማ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የቱሪዝም ልማት ሥራዎች ለዘርፉ ዕድገት ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ ነው
Jan 8, 2026 50
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የቱሪዝም መስህብ ልማት ሥራዎች ምቹ የመዳረሻ ምህዳር እየፈጠሩ መሆናቸውን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ገለጸ። ጅማ ዞን በሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ ሀብት እምቅ አቅም ያለው ሲሆን በኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ጅማ ከፍተኛ ጥራት ያለው የቡና ምርት ከሚገኝባቸው ቀጠናዎች አንዱ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የቡና ማሳዎችንና የዝግጅት ሂደቶችን ለጎብኚዎች ክፍት በማድረግ የቡና ቱሪዝምን ለማሳደግ እየተሠራ ይገኛል። በዞኑ የሚገኘው የደን ሽፋን ለአካባቢ ተስማሚ ቱሪዝም ወይንም ኢኮ-ቱሪዝም ትልቅ ዕድል ያለው ነው፡፡ የጅማ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ኒሜሪ አባተማም ለኢዜአ እንደገለጹት፤ እያንዳንዱ ወረዳ ቢያንስ አንድ የቱሪስት መዳረሻ እንዲኖረው ሰፋፊ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ እስካሁንም በ21 አዳዲስ ግንባታ ከተጀመረባቸው ወረዳዎች መካከል የሦስቱ ተጠናቀው ለተጠቃሚ ክፍት መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ እነኚህም ነዲ ጊቤ፣ ሊሙ ኮሳ እና ሊሙ ገነት ወረዳዎች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በሌሎቹም ቦታ የመለየት፣ በጀት የመያዝ እንዲሁም የማልማት ስራዎች መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡ በዞኑ የሚገኙ እምቅ የቱሪዝም መስህቦችን ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች በማስተዋወቅ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡ የቱሪስት ፍሰቱን ለመጨመርና የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም መሠረተ ልማት ወሳኝ በመሆኑም በጅማ ከተማ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች እንዲገነቡ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በዞኑ በሚገኙ ቀበሌዎች የመንገድ መሠረተ ልማት የማሟላት ሥራ መከናወኑን ጠቁመው፤ የመዳረሻ ልማቱ ከኮሪደር ልማት ጋር በመሰናሰል እስከ አርሶ አደር ቀዬ እንዲደርስ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ እነዚህ የልማት ሥራዎች የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው፤ ዘርፉን በዘላቂነት ለማሳደግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሠሩ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ ይህም ዞኑን ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ በማድረግ የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ጠቁመዋል።
የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህንን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Jan 8, 2026 49
ደብረ ማርቆስ ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህንን ተደራሽ በማድረግ የማህበረሰቡን ጤና ለመጠበቅ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ጤና መምሪያ ገለጸ። የመምሪያው ሃላፊ አቶ የሽዋስ አንዷአለም ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የማህበረሰቡን ጤና ለመጠበቅ ለቅድመ መከላከልና ህክምና ጥራትን ማስጠበቅ ላይ በቅንጅት እየተሰራ ነው። ለዚህም በበጀት ዓመቱ ከ500 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች የማህበረሰብ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ መታቀዱን አንስተዋል። እቅዱን ለማሳካት በተደረገው ጥረት በበጀት ዓመቱ አምስት ወራት ከ200 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። የጤና መድህን አገልግሎቱ ዜጎች አንድ ጊዜ በከፈሉት አነስተኛ ገንዘብ የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ጤና ለመጠበቅ ማገዙንም ጠቁመዋል። የአገልግሎቱን ፍትሃዊነት ለማረጋገጥም መክፈል ለማይችሉ ከ188ሺህ በላይ ወገኖች መንግስት ከ36 ሚሊዮን ብር በላይ በመደጎም ነጻ ህክምና እንዲያገኙ ማድረጉን አስረድተዋል። ቀደም ሲል በአገልግሎት አሰጣጡ የሚታይ የነበረን የመድሃኒት አቅርቦት ችግር ለመፍታትም በሁሉም ወረዳዎች የማህበረሰብ መድሃኒት ቤቶችን ለማስፋት እየተሰራ ነው ብለዋል። በዞኑ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች መካከል የጎዛምን ወረዳ የቡቅላ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ የውብ ምርት መለሰ ፤ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል በመሆናቸው የቤተሰባቸውን ጤና ለመጠበቅ እንደቻሉ አስረድተዋል። በአንድ ጊዜ አነስተኛ መዋጮ ዓመቱን ሙሉ ያለ ስጋት እንዲታከሙ በማድረጉና በአካባቢያቸው የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት መቋቋሙ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻሉን ጠቁመዋል። በዞኑ ባለፈው ዓመት ከ442 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን በማቀፍ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለኢንተርፕራይዞች የሚሰጠው የክህሎት ማበልጸጊያ ስልጠና ውጤታማነትን እያሳደገ ነው
Jan 8, 2026 63
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኢንተርፕራይዝ ለተሰማሩ ዜጎች የሚሰጠው የክህሎት ማበልጸጊያ ስልጠና ውጤታማነትን እያሳደገ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ገለጹ። የአዲስ አበባ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከመደበኛ መማር ማስተማር ተልዕኳቸው ጎን ለጎን የወጣቶችን የሥራ ውጤታማነት የሚያዳብር የክህሎት ማበልጸጊያ ሥልጠናዎችን በመስጠት ላይ ይገኛሉ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ አመራሮችም፤ የመዲናዋን ኢንተርፕራይዞች ውጤታማነት የሚያሳድግ ተከታታይ የክህሎት ድጋፍ ስልጠና እየሰጡ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የደጃዝማች ገረሱ ዱኪ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዋና ዲን መስፍን ቸሩ፤ የኢንተርፕራይዞችን ምርታማነት የሚያጎለብት በክህሎት የበለጸገ የሰው ሃይል የማፍራት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በተለይም በአውቶሞቲቭ፣ ሆቴልና ቱሪዝም፣ ጨርቃ ጨርቅና የቆዳ ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የኢንተርፕራይዞችን የምርትና አገልግሎት ጥራት የሚያስጠብቅ የክህሎት ስልጠና እየተሰጠ ነው ብለዋል። የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዋና ዲን ቢንያም አወቀ (ዶ/ር)፤ በአሁኑ ወቅት የ1ሺህ 100 ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማነት የሚያሻሽል የክህሎት ማበልጸጊያ ስልጠና እየተሰጠ ነው ብለዋል። የኢንተርፕራይዝ ድጋፍና ክትትልም የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን የተመዘገቡ ውጤቶችን በጥናትና ምርምር በመለየት ውስንነቶች እንዲቀረፉላቸው የማድረግ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን ሸላማ ንጉሱ፤ ለኢንተርፕራይዞች የሚሰጠው የክህሎት ማበልጸጊያ ስልጠና የአምራች ኢንዱስትሪ ሽግግሩን በማሳለጥ በተኪ ምርት ውጤት እየተገኘ ነው ብለዋል። በማኑፋክቸሪንግ፣ ከተማ ግብርናና መሠል መስኮች ለተሰማሩ ኢንተርፕራዞች ውጤታማ ማኅበራትን ማፍራት ያስቻለ ስልጠና እየተሰጠ እንደሚገኝም ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ከተማ የሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ኃላፊ ሚደቅሳ ከበደ፤ የኮሌጆች የክህሎት ማበልፀጊያ ስልጠና ለኢንተርፕራይዞች ውጤታማነት መሰረት ነው ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችም የሥራ ፈላጊ ዜጎችን የክህሎት ዝንባሌ ታሳቢ በማድረግ የሚሰጡት ትምህርትና ስልጠና ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
በኦሮሚያ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁለንተናዊ ልማትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Jan 8, 2026 33
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁለንተናዊ ልማትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ገለጹ። በክልሉ እስካሁን ከ22ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውን አስታውሰው ሰላምን በመግፋት በጥፋታቸው በቀጠሉት ላይ ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ፤ የክልሉን ወቅታዊ የሰላምና የልማት እንቅስቃሴ በማስመልከት ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የክልሉ መንግስት ከለውጡ ወዲህ ከገጠሙት ፈተናዎች መካከል በተወሰኑ አካባቢዎች የጸጥታ ችግር እንደነበር አስታውሰው በዘላቂነት ለመፍታት ብዙ መሰራቱን አስረድተዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን ከማስከበር በተጓዳኝ የተሳሳተ መንገድ ላይ የነበሩ አካላት ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ጥረት ተደርጓል ብለዋል። ከመንግስት የሰላም ጥሪ ባለፈ በአባ ገዳዎች፣ በሃዳ ሲንቄዎች፣ በሃይማኖት አባቶች እና በሀገር ሽማግሌዎች አማካኝነት ለሰላም ምላሽ እንዲሰጡ መሰራቱን አንስተዋል። በዚህም መሰረት ከ22 ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪን በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ሰላማዊ ህይወት መመለሳቸውን ገልጸዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል 10ሺህ የሚሆኑት የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ሲሆን ሌሎች እንደየፍላጎታቸው ወደ መደበኛ ህይወታቸው ተመልሰዋል ብለዋል። የመስሪያ ቦታ እና 581 ሚሊዮን ብር ብድር ተመቻችቶላቸው ወደ ስራ የገቡ እንዳሉ ገልጸው ወደ ትምህርት እና ወደ መንግስት ስራም የተመለሱ እንዳሉ ጠቅሰዋል። በክልሉ የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁለንተናዊ ልማትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል። “በጽንፈኝነት ለጥፋት ዓላማ የተሰለፈ ሁሉ የትኛውንም ቋንቋ ቢናገር ጽንፈኛ ነው” ያሉት አቶ ሃይሉ የኦሮሞም ይሁን የአማራ ጽንፈኛ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ይጠናከራል ብለዋል። በቅርቡ በሆሮ ጉዱሩ እና ምስራቅ ወለጋ ዞኖች የተወሰኑ አካባቢዎች በጽንፈኞች ላይ ጠንካራ እርምጃ በመወሰዱ በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።
በወራቤ ከተማ ከዘጠኝ ሄክታር መሬት በላይ የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ የኮሪደር የልማት ሥራ እየተፋጠነ ነው
Jan 8, 2026 49
ወራቤ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በወራቤ ከተማ ከዘጠኝ ሄክታር መሬት በላይ የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተፋጠነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ያሲን ከሊል ገለጹ፡፡ ከንቲባው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከተማዋን ውብ፣ ፅዱ እንዲሁም ለኑሮ እና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ከዚህም ውስጥ አንዱ የወንዝ ዳርቻ ልማት መሆኑን ጠቅሰው በከተማ አስተዳደሩና በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከ9 ሄክታር በላይ የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ ልማት ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል። የወንዝ ዳርቻ የኮሪደር ልማት ሥራው የከተማውን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ምቹ የመኖሪያ አካባቢ እየፈጠረ መሆኑን ጠቅሰው የልማት ስራውን በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ከልማት ሥራው በተጨማሪ የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣ ካፍቴሪያ፣ የቅርጫትና የመረብ ኳስ መጫወቻ ሜዳ ፋውንቴን እንዲሁም ሰው ሰራሽ አነስተኛ ሐይቅ ማካተቱን ጠቅሰው የእነዚህ ግንባታዎች ስራም እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመዋል። ከ2 ሺህ 500 በላይ ሰዎችን መያዝ የሚችል ቲያትር አዳራሽ፣ የእግር ኳስ ሜዳና ሌሎች የግንባታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወጣት አብዲ ዋሴ እና አቶ ሸርፈዲን ሹሜ፤ የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራው የወራቤ ከተማን ለነዋሪው ምቹ እንድትሆን ከማድረግ በተጨማሪ ከሌሎች አቻ ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ እንደሚያደርጋት ተናግረዋል። በተለይም በከተማዋ የወንዝ ዳርቻን ለማልማት የተጀመረው ሥራ አካባቢው ቀድሞ የነበረውን መጥፎ ገጽታ በመቀየር ለመዝናኛና ለሥራ ዕድል እንዲውል መደረጉን ገልጸዋል። በከተማዋ እየታየ ያለው ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እያደረግን ያለውን ድጋፍ አጠናክረን እንቀጥላለን ነው ያሉት ነዋሪዎቹ።
በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሠረት ዕሴት የታከለበት ቡናን መላክ ተጀምሯል
Jan 8, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሠረት ዕሴት የታከለበት የኢትዮጵያ ቡናን ለአፍሪካ ሀገራት ገበያ መላክ መጀመሩን የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ። የአፍሪካ ሕብረት መረጃ እንደሚያሳየው የአፍሪካ ሀገራት 85 በመቶ ምርታቸውን ለአውሮፓ፣ እስያ፣ ሰሜንና ላቲን አሜሪካ ገበያ የሚልኩ ሲሆን በአንፃሩ የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጣቸው ከ15 በመቶ ያልበለጠ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራም የሀገራቱን የእርስ በእርስ የንግድ ትስስር በማሳለጥ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን እንደሚያሳድግ ታምኖበታል። አህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነቱም የአፍሪካ ሀገራትን የንግድ ታሪፍና መሰናክል በማስወገድ ወጥ በሆነ የአሰራር ሥርዓት የእርስ በእርስ የገበያ ትስስርን ማሳለጥ ዋና ዓላማው ያደረገ ነው። ይህም የአህጉሪቷን አባል ሀገራት የንግድ ልውውጥ በማሳደግ፣ የኢንዱስትሪ ዕድገትን በማፋጠንና ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የአፍሪካን ኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማሳለጥ ከፍተኛ ፋይዳ አለው። በዚህም ኢትዮጵያ በአህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነቱ መሰረት ከመስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ገበያ የንግድ ምርቶችን መላክ ጀምራለች። የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ዑመር ለኢዜአ እንዳሉት፤ በአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ሥምምነት መሰረት የኢትዮጵያ ቡና ገበያ መዳረሻን ለማስፋት እየተሰራ ነው ። የአፍሪካን ሰፊ የገበያ ዕድል ለመጠቀም የኢትዮጵያን ጥሬ ቡና ከመላክ ይልቅ ዕሴት ጨምሮ ማቅረብ ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል። በዚህም በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት ዕሴት የተጨመረበት ቡናን የመላክ ጅማሮ የበለጠ ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ አዳዲስ የቡና ገበያ መዳረሻዎችን እያሰፋች ነው ያሉት አቶ ሻፊ፤ ለአብነትም በ2016 ዓ.ም 64 ሀገራት የነበረውን የኢትዮጵያን የቡና ገበያ መዳረሻ በ2017 ዓ.ም ወደ 84 ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። የኢትዮጵያን ነባር የቡና ገበያ መዳረሻ በማጠናከርና አዳዲስ ገበያን ለማስፋት በተለያዩ ሀገራት ከሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቻይናን ጨምሮ አስር የእስያ ሀገራት የኢትዮጵያን ቡና እየገዙ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በቀጣይም ቡና ላይ ዕሴት በመጨመር የአፍሪካና እስያ ገበያን ለመጠቀም ከኢትዮጵያ ቡና ላኪዎችና የአውሮፓ ባለሃብቶች ጋር በመቀናጀት ዕሴትን ጨምሮ መላክ ላይ እንዲሳተፉ ይሰራል ብለዋል።
በድሬዳዋ በዘንድሮው የበጋ ወራት ከ3 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ እየለማ ነው
Jan 8, 2026 94
ድሬዳዋ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በዘንድሮው የበጋ ወራት ከ3 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም የአስተራረስ ስነ-ዘዴ በመስኖ እየለማ መሆኑን የአስተዳደሩ ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ገለፀ። የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ሚስራ አብደላ፣ባሳለፍነው ክረምት እና በበጋ ወራት በአነስተኛ መስኖ ልማቶች የተገኙ ውጤቶችን እና ቀጣይ ተግባራትን አስመልክተው ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ወይዘሮ ሚስራ እንዳሉት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በአስተዳደሩ የገጠር ቀበሌዎች የተከናወኑ የተቀናጁ የግብርና ልማት ስራዎች የተረጂነትና የጠባቂነት አስተሳሰብን በመናድ ተጨባጭ ውጤቶች እያመጡ ናቸው። በተለይም የተከናወኑ የተፋሰስ፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር፣ የአነስተኛ መስኖና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡ የምግብ ሉዓላዊነት እንዲረጋገጥ ማስቻላቸውን ተናግረዋል። በአስተዳደሩ የገጠር ክላስተሮች የተከናወኑት የልማት ስራዎች በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ ማምረት ባህል እንዲሆን ማስቻላቸውን ጠቁመው፤ በዘንድሮው የበጋ ወራትም በ3 ሺህ 254 ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም የሆርቲካልቸር ልማት እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። በበጋው እየለሙ የሚገኙት የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የቡና ማሳዎች የሚፈለገውን ውጤት እንዲያስገኙ ለአርሶ አደሩ፣ ለግብርና ባለሙያዎች እና አመራሮች የተሰጠው ስልጠና ወሳኝና ቅንጅታዊ የአስራር ባህል እንዲዳብር ማድረጉን አንስተዋል። ይህም ልማት በመጋቢት ወር መጨረሻ 839 ሺህ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ያስችላል ብለዋል። በመጪው ጥር ወር የሚጀመረው የዘንድሮው የበጋ ተፋሰስ ልማትም የመስኖ ልማቱን ውጤታማነት ከማጠናከር ባሻገር አርብቶ አደሩ ከእንሰሳት ሃብቱ ይበልጥ ተጠቃሚ እንዲሆን ያስችላል ብለዋል። የአዲጋ ፈለማ የገጠር ቀበሌ አርሶ አደር መሐመድ ኢብራሂም፤ የተጀመረው የተፋሰስ እና የመስኖ ልማት ስራ ማህበረሰቡን ከተረጂነት በማላቀቅ የምግብ ሉዓላዊነት እንዲያረጋግጥ እያገዙ መሆኑን ገልፀዋል። ከቀናት በኋላ የሚጀመረውን የተፋሰስ ልማት ስኬታማ ለማድረግ የሚያስችሉ ዝግጅቶች ተጠናቀው ወደ ስራ ለመግባት እየተጠባበቁ መሆኑንም ተናግረዋል። ከድሬዳዋ አስተዳደር ህዝብ አንድ ሶስተኛውን እና የአስተዳደሩን መልክዓ ምድር 96 በመቶ የሚሸፍነው የገጠሩን ህብረተሰብ የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ በመተግበር ላይ የሚገኙት የልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑም ተገልጿል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያ ሳተላይቶች ያመነጯቸው መረጃዎች ጉልህ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አበርክተዋል
Jan 8, 2026 60
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሳተላይቶች ያመነጯቸው መረጃዎች ጉልህ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማበርከታቸውን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ገለጸ። በሚቀጥለው ዓመትም ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ የመረጃ ሳተላይት ወደ ሕዋ ለማምጠቅ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል። የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን ሳተላይት ኢቲ-አር.ኤስ.ኤስ1 (ET-RSS1) እንዲሁም ሁለተኛው ኢቲ-ስማርት-አር.ኤስ.ኤስ (ET-SMART-RSS) የተሰኙ ሁለት የመረጃ ሳተላይቶችን ወደ ሕዋ ማምጠቋ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ቀደም ሲል ወደሕዋ የተላኩ ሁለት የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች የአገልግሎት ጊዜያቸውን አጠናቀዋል። የመሬት ምልከታ የመረጃ ሳተላይቶቹም በርካታ ቴክኖሎጂያዊና ሳይንሳዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን ማበርከታቸውን ተናግረዋል። በዚህም የምግብ ዋስትና፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በተፈጥሮ ሃብት አያያዝ የግብርና መስኮች፣ በከተማ ፕላንና መሠረተ ልማት፣ በሀገር ሉዓላዊነትና ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ጠቀሜታ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም በሚቀጥለው ታኅሳስ 2019 ዓ.ም በምስል ጥራትና የጊዜ ቆይታ አቅም ያላት ኢቲ-አር.ኤስ.ኤስ 2 (ET-RSS2) የተሰኘች ሳተላይት ወደ ሕዋ ለማምጠቅ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። በቀጣይ የምትመጥቀው ኢቲ-አር.ኤስ.ኤስ 2 ሳተላይት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመታጠቅ በሕዋ ላይ የአምስት ዓመታት የጊዜ ቆይታ እንዲኖራት ታሳቢ መደረጉ ነው የተገለጸው። ከዚህ ቀደም ወደ ሕዋ ከተላኩ ሳተላይቶች የተገኘውን መረጃ የመቀበል፣ የመተንተን፣ የመቆጣጠርና የጥገና አቅም መፈጠሩን አስረድተዋል። ሦስተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ እየተደረገ የሚገኘው ጥረትም የኢትዮጵያን የሳተላይት ልማት አቅም በተግባር የሚያሳይ እንደሚሆን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረት እየጣለች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jan 6, 2026 133
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የፖሊሲ ማዕቀፍ እና መሰረተ ልማትን ጨምሮ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረት የሚጥሉ ስራዎችን እያከናወነች እንደምትገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በማስመልከት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሑፍ አቅርበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ ከምሁራን ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤ.አይ) በዓለም ደረጃ ያለው ተጽእኖ እና ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። በተጠናቀቀው የ2025 የፈረንጆቹ ዓመት ኤ.አይ በርካታ ስራዎችን መተካቱን አውስተው አሁንም በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ፈጥነን ልጆቻችንን ካዘጋጀን ሰው ሰራሽ አስተውሎትን እንደ ተለያዩ ምርቶች በቀላሉ መጠቀም እንችላለን ብለዋል። ኤ.አይ ስራ ይቀማል ብዬ አልሰጋም ሲሉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሰው ልጅ መስራት የሰው ልጅ ሊሰራቸው የማይገባቸውን ስራዎች እየተካ ይሄዳል ነው ያሉት። ኤ.አይን የምንፈጥር እኛነን ኤ.አይን የምንቀይር እኛ ነን ቀድመን ግን ፋውንዴሽን መጣል ይገባናል ብለዋል። መንግስት ለሰው ሰራሽ አስተውሎት ፖሊሲ እና ስትራቴጂ አዘጋጅቶ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው ሳይንስ ሙዚየም አንዱ መሰረተ ልማት መሆኑን ተናግረዋል። መሰረተ ልማት እና ታለንት ለዘርፉ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱም ነው ያብራሩት። ኢትዮጵያ የምትገነባው የኤ.አይ ዩኒቨርሲቲም የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን ብዙ ችግሮች ይፈታል ተብሎ እንደሚታመን ተናግረዋል። ዋናው ለልጆቻችን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልጆቻችን የሚወዳደሩበት ልጆቻችን ከሌላው አንስው የማይታዩበት ሁኔታ ለመፍጠርም እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ቀድሞ መወዳደር ቀድሞ መገኘት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ኤ.አይን በዛ መልክ ማየት እንደሚገባ ገልጸዋል። ኤ.አይ ስራዎችን በማቃለል እና ጊዜ በመቆጠብ ወሳኝ ድርሻ እንደሚወጡም ነው የገለጹት። ተማሪዎችም ኤ.አይን መጠቀም አለባቸው፤ ቴክኖሎጂዎቹን መጠየቅ እንዲችሉ አድርገን ከፈጠርናቸው ተማሪዎች ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉ ገልጸዋል። የመጠየቅ ብቃት ችሎታ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ረገድም ኤ.አይ የተማሪዎችን አቅም እንደሚገነባ ተናግረዋል። የመጀመሪያው ትውልድ ለኢኮኖሚ ቅድሚያ የሰጠ እና ሁለተኛው ትውልድ ፖለቲካዊውን ያስቀደመ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሁኑ ዘመን የሀሳብ ትውልድ እንደሆነም ጠቅሰዋል። ሀሳብ የሚወድ ትውልድ ችግሮች እየፈታ እና እያቀለለ እንደሚሄድም ተናግረዋል። ኤ.አይ ዝግጅት እና ስራ እንደሚፈልግ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከመፍራት ይልቅ እውነታውን በመጋፈጥ ማሸነፍ እንችላለን ብለዋል።
ከተማርንና ዝግጁ ከሆንን በኤ አይ የማይናቅ ደረጃ ላይ እንደርሳለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jan 6, 2026 100
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018(ኢዜአ)፡- ከተማርንና ዝግጁ ከሆንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት የማይናቅ ደረጃ ላይ እንደርሳለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በማስመልከት በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ጽሑፍ አቅርበዋል። ጽሑፍ ካቀረቡ በኋላም ከምሁራን ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም፤መንግሥት የኮሪደር ልማትና መንገድ ሠርቶ ለነዋሪው ሲያቀርብ ይህን በአግባቡ እንዴት መያዝ እንደሚቻል ደግሞ ምሁራን ከተሜነትን የሰው ልጅ ዐዕምሮ ላይ መሥራት ይጠበቅባችኋል ብለዋል። ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር በተያያዘም ኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋ ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል። ኤ አይ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ ኢነርጂ መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ ብዙ የማምረት ዐቅም እንዳላት አረጋግጠዋል። ኢነርጂ ላይ ኢንቨስት ካደረግን ለኤ አይ አንድ አስቻይ ጉዳይ ፈታን ማለት ነው ሲሉም ገልጸዋል። ሌላው ኤ አይ የሚፈልገው ጉዳይ መረጃ(ዳታ) እና የመረጃ ማዕከል(ዳታ ሴንተር) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ከተማርን፣ ዝግጁ ከሆንን፣ እየሠራናቸው ያሉትንና በቀጣይ የምናከናውናቸውን ጨምሮ በመተባበር ለለውጥ ዝግጁ ሆነን በትጋት ከሠራን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት የማይናቅ ደረጃ ላይ እንደርሳለን ብለዋል። ለኤ አይ ግብዓት የሚሆኑ ነገሮች በብዛት በአፍሪካ እንደሚገኙም አስገንዝበዋል።
ማዕከሉ በምርምር ያወጣቸውን የሰብል ዝርያዎችን ተደራሽ ለማድረግ የመነሻ ዘር ብዜት እያካሄደ ነው
Jan 5, 2026 166
ሮቤ፤ ታህሳስ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሲናና ግብርና ምርምር መዕከል በምርምር ያገኛቸውን የተለያዩ የሰብል ዝርያዎች ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ የመነሻ ዘር እያባዛ መሆኑን ገለጸ። ማዕከሉ አርሶ አደሮችና የባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የመስክ ቀን ጉብኝት አካሂዷል። በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የምርምር ማዕከሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ታመነ ሚደቅሳ እንዳሉት፤ማዕከሉ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በምርምር እየደገፈ ነው። በተለይ ማዕከሉ ባለፉት ዓመታት በስንዴ፣ ገብስና ሌሎች ስምንት የትኩረት መስኮች ላይ ተመስርቶ ምርምሮችን በማካሄድ 116 የምርምር ውጤቶችን ለተጠቃሚው ማድረሱን አስታውሰዋል። ማዕከሉ በቅርብ ጊዜ በምርምር ያወጣቸውን ዝርያዎች አርሶ አደሩ ጋር ተደራሽ እንዲሆኑ የመስራች ዘር የማባዛት ሥራ እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። በሲናና አርሶ አደሮች በኩታገጠም አሰራር እየተባዛ ያሚገኘውና አርሶ አደሩ ልምድ እንዲለዋወጥ ዓላማ በማድረግ የተዘጋጀው የመስክ ምልከታ የዚሁ ጥረት አካል ነው ብለዋል። በማዕከሉ የግብርና ኤክስቴንሽን ተመራማሪ አቶ ባያታ ጋዲሳ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ በምርምር የሚያወጣቸው የሰብል ዝርያዎች ውጤታማነታቸው ከተረጋገጠ በኋላ አርሶ አደሩ ጋር ተደራሽ እንደሚሆኑ አመልክተዋል። ዝርያዎቹ በስፋት ተጠቃሚው አርሶ አደር ጋር እንዲደርሱ በምርምር ማዕከሉና በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ በማባዛት ተደራሽ እንደሚደረጉ አክሏል። አቶ ባያታ እንዳሉት፤ ማዕከሉ በአሁኑ የመኽር ወቅት በምዕራብ አርሲና በባሌ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ከ150 ሄክታር በሚበልጡ የአርሶ አደሩ ማሳ ላይ በቅርቡ ከማዕከሉ የተለቀቁ ዝርያዎችን እያባዛ መሆኑን አስረድተዋል። እየተባዙ ከሚገኙ ዝርያዎች መካከል በአንድ ሄክታር መሬት እስከ 72 ኩንታል ምርት የሚሰጥ ''ቦኩ'' የሚባል ስያሜ የተሰጠው የስንዴ ዝርያ እንደሚገኝበት አመልክተዋል፡፡ የመስክ ምልከታው ላይ የተሳተፉ አርሶ አደሮች በሰጡት አስተያየት፤ ማዕከሉ በአካባቢያቸው በመኖሩ የተሻለ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በየጊዜው በማግኘት ምርታማነታቸውና ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። በ1978 ዓ.ም የተቋቋመው የሲናና ግብርና ምርምር ማዕከል እስከ አሁን 116 የሚሆኑ የሰብል፣ የእንስሳት መኖና ሌሎች የግብርና ቴክኖሎጂዎች ላይ ያተኮሩ ዝርያዎችን በምርምር በማፍለቅ ለተጠቃሚው ማሰራጨቱ ተገልጿል።
ስፖርት
ነጌሌ አርሲ ተከታታይ አራተኛ ድሉን አስመዘገበ
Jan 8, 2026 46
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ነጌሌ አርሲ ምድረ ገነት ሽሬን 1 ለ 0 አሸንፏል። የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ይጫወታል አሁናዊ ቁጥራዊ መረጃዎች ስለ 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ከቤ ብዙነህ በ12ኛው ደቂቃ ላይ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ነጌሌ አርሲ በ25 ነጥብ ደረጃውን ከሶስተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ምድረ ገነት ሽሬ በ17 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። የማድሪድ ደርቢ በስፔን አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል እና ሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
አሁናዊ ቁጥራዊ መረጃዎች ስለ 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 8, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ወደ ሩብ ፍጻሜው ተሸጋግሯል። በውድድሩ እስከ አሁን በተደረጉ 44 ጨዋታዎች 87 ግቦች ከመረብ ላይ አርፈዋል። ይህም በአማካይ በአንድ ጨዋታ 1 ነጥብ 98 ጎል ይቆጠራል ማለት ነው። ናይጄሪያ 12 ግቦችን በውድድሩ ላይ በማስቆጠር ቀዳሚውን ስፍራ የያዘች ሀገር ናት። በተጨማሪም 64 የግብ ሙከራዎች (30 ኢላማቸውን የጠበቁ) ሙከራዎችን በማድረግ ከፍተኛውን ድርሻ ይዛለች። በተጨማሪም ናይጄሪያ በየጨዋታው የ66 በመቶ የኳስ ድርሻ በመያዝ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከፍተኛውን ድርሻ የያዘች ሀገር ሆናለች። ቦትስዋና፣ ጋቦን እና ዩጋንዳ በተመሳሳይ ሰባት ጎሎችን በማስተናገድ በርካታ ግብ የተቆጠረባቸው ሀገር መሆናቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስታውቋል። የሞሮኮው ብራሂም ዲያዝ አራት ግቦችን በማስቆጠር የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። የናይጄሪያው አዴሞላ ሉክማን አራት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል በርካታ የግብ እድሎችን ፈጥሯል። እስከ አሁን በተደረጉ 44 ጨዋታዎች 173 ቢጫ ካርድ እና ሰባት ቀይ ካርዶች ተመዝግበዋል። ከነዚህም ውስጥ ማሊ 11 ቢጫ እና ሁለት ቀይ ካርዶችን በመመልከት የቀዳሚውን ስፍራ ይዛለች። ማሊ እና ቱኒዚያ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ በተመሳሳይ ሁለት የፍጹም ቅጣት ምቶችን በማግኘት በግንባር ቀደምትነት ይቀመጣሉ። የአዘጋጇ ሞሮኮ ተጫዋቾች እስከ አሁን ባደረጓቸው ጨዋታዎች 77 ጊዜ ጥፋት በመፈጸም ጥሩ ያልሆነ ክብረ ወሰን ይዘዋል። የሞሮኮ እና የደቡብ አፍሪካ ተጫዋቾች በተመሳሳይ 10 ጊዜ ከጨዋታ ውጪ በመሆን ብዙ ጊዜ ከጨዋታ ውጪ የሆኑ ተጫዋቾችን የያዙ ሀገራት ሆነዋል። የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሃ ግብር ጥር 1 እና 2 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። አጠቃላይ ውድድሩም እስከ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። በቀሪ ስምንት ጨዋታዎች በአሃዛዊ መረጃዎች ላይ ለውጦች እንደሚኖሩ ይጠበቃል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ይጫወታል
Jan 8, 2026 91
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ዛሬ በሚደረጉ ጨዋታዎች ይጀመራል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሲዳማ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ጨዋታውን ያደርጋል። ሲዳማ ቡና በሊጉ ባደረጋቸው 13 ጨዋታዎች መካከል ስምንቱን ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በአራት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በ13ቱ ጨዋታዎች ላይ 18 ጎሎችን ሲያስቆጥር ስድስት ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ28 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው አርባምንጭ ከተማ በሊጉ ምንም ጨዋታ ያለሸነፈ ብቸኛ ቡድን ነው። ስድስት ጊዜ ሲሸነፍ በሰባቱ አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ ላይ አምስት ግቦችን ሲያስቆጥር 14 ጎሎችን አስተናግዷል። አርባምንጭ ከተማ በሰባት ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃን ይዟል። ሲዳማ ቡና ካሸነፈ የሊጉን መሪነት ያጠናክራል። አርባምንጭ ከተማ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። በሌላኛው መርሃ ግብር ምድረገነት ሽሬ ከነጌሌ አርሲ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። ምድረገነት ሽሬ እስከ አሁን በሊጉ 13 ጨዋታዎችን አድርጎ አራት ጊዜ ሲያሸንፍ በተመሳሳይ በአራቱ ተሸንፏል። አምስት ጊዜ ነጥብ ጥሏል። 11 ግቦችን ሲያስቆጥር ዘጠኝ ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ17 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። አዲስ አዳጊው ነጌሌ አርሲ በሊጉ ባከናወናቸው 13 ጨዋታዎች በስድስቱ ሲያሸንፍ በሶስቱ ሽንፈት አስተናግዷል። አራት ጊዜ አቻ ወጥቷል። 15 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ዘጠኝ ግቦች ተቆጥረውበታል። ነጌሌ አርሲ በ22 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ምድረገነት ሽሬ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ ነጌሌ አርሲ በድል ጉዞው ለመቀጠል ይጫወታሉ። ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከአዳማ ከተማ ከቀኑ 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ10 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። አዳማ ከተማ በ21 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ጨዋታው ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው።
የማድሪድ ደርቢ በስፔን አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ
Jan 8, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በስፔን የአሸናፊዎች ዋንጫ አትሌቲኮ ማድሪድ እና ሪያል ማድሪድ ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ጨዋታው ምሽት አራት ሰዓት ላይ በኪንግ አብደላ ስፖርትስ ስታዲየም ይካሄዳል። ሁለቱ ክለቦች በስፔን የአሸናፊዎች ዋንጫ ሲገናኙ የአሁኑ ለአምስተኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም በተደረጉት አራት ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ ሁለት ጊዜ ሲያሸነፍ አትሌቲኮ ማድሪድ በአንዱ ድል ሲቀናው በአንዱ ጨዋታ አቻ ተለያይቷል። ሁለቱ ቡድኖች ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት እ.አ.አ በ2024 በግማሽ ፍጻሜ ሲሆን በወቅቱ ሪያል ማድሪድ 5 ለ 3 በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፏል። በወቅቱ ሪያል ማድሪድ በፍጻሜው ባርሴሎናን 4 ለ 1 በማሸነፍ ዋንጫ አንስቷል። ከአራቱ ጨዋታዎች አንዱ (እ.አ.አ በ2014) ፍጻሜው በደርሶ መልስ ሲካሄድ የተደረገ ነው። ሪያል ማድሪድ የስፔን አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫን 13 ጊዜ ሲያነሳ አትሌቲኮ ማድሪድ ሁለት ጊዜ ውድድሩን አሸንፏል። የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ በፍጻሜው ከባርሴሎና ጋር ይጫወታል። ባርሴሎና ትናንት አትሌቲኮ ቢልባኦን 5 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የፍጻሜው ጨዋታ እሁድ ጥር 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የስፔን የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ በስፔን ላሊጋ እና በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ በተመሳሳይ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃን የያዙ ክለቦች የሚሳተፉበት ውድድር ነው።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገቷን ከካርቦን ልቀት ነጻ ለማድረግ ዓርአያነት ያለው ተግባር እያከናወነች ነው
Jan 8, 2026 38
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገቷን ከካርቦን ልቀት ነጻ ለማድረግ ለታዳጊ ሀገራት ትልቅ ትምህርት እየሰጠች መሆኗን ዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጀንሲ ገለጸ። አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) በዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ ሆነው የተሰየሙበትን የሹመት ደብዳቤ ለተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ፍራንቸስኮ ላ ካሜራ አቅርበዋል፡፡ በዚሁ ወቅትም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) የተላከን መልዕክት ማቅረባቸው ተገልጿል። ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፉ የኃይል ሽግግር ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነትም ለዋና ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል። ሀገራችን ከምትጠቀመው የኃይል ምንጭ ውስጥ ከ90 በመቶ የሚልቀው ከታዳሽ ኃይል የሚገኝ ነው ያሉት አምባሳደሩ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል መሆኗን አስረድተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የንፋስ፣ የፀሐይ እና የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች ለቀጣናው የኃይል ዋስትና እና ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም እያበረከቱት ያለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦም አስገንዝበዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ ተነሳሽነት እና ወደ ዝቅተኛ የካርቦን ኢኮኖሚ የምታደርገው ሽግግር ለመላው የአፍሪካ አኅጉር ዘላቂ ልማት እንደ ማሳያ የሚያገለግል መሆኑንም አመላክተዋል። ዋና ዳይሬክተር ፍራንቸስኮ ላ ካሜራ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በዘላቂ ልማት ዘርፍ እያሳየች ያለውን ዓርአያነት ያለው አመራር አድንቀው፤ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገቷን ከካርቦን ልቀት ነጻ ለማድረግ ለታዳጊ ሀገራት ትልቅ ትምህርት እየሰጠች ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) እንድታስተናግድ መመረጧ ለዓለም አቀፉ የአየር ንብረት አጀንዳ ያላትን የላቀ ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም በአድናቆት አንስተዋል። ኤጀንሲው ኢትዮጵያ ቅድሚያ በምትሰጣቸው የኃይል ፕሮጀክቶች የቴክኒክ ድጋፍ ለመስጠት እና የኢንቨስትመንት ፋይናንስ ለማሰባሰብ ቁርጠኛ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በዞኑ የተራቆቱ አካባቢዎችን በአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው
Jan 8, 2026 74
ነገሌ ቦረና፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን የተራቆቱ አካባቢዎችን በአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የደን ጥበቃ የስራ ሂደት ቡድን መሪ አቶ አልዬ አረባ እንዳሉት፤ በዞኑ የተራቆቱ አካባቢዎችን በአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው። በአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራውም ከ52 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት የሚሸፍኑ 105 ተፋሰሶች እንደሚለሙ አስረድተዋል፡፡ የተፋሰስ ልማቱን ለማሳካትም 379 የቀበሌ አመራሮችና የልማት ጣቢያ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በዞኑ የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ስራው ከ226 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል፡፡ በበጋ ወራቱ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ እርከንን ጨምሮ ከእንስሳትና ሰው ንኪኪ ነጻ በማድረግ በመጪው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ ልማት ለመሸፈን መታቀዱን ተናግረዋል። የተራቆተና የተጎዳ 38 ሺህ 244 ሄክታር የግጦሽ ሳር መሬት ከንክኪ የመከለል ስራም የተፋሰስ ልማቱ አካል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ከበጋው ወራት የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ ጎን ለጎን በክረምቱ የሚተከሉና ጥምር ጥቅም የሚሰጡ 36 ሚሊዮን ችግኞችን የማፍላት ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ልማት ስራዎች በዞኑ ድርቅን በመቋቋም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የራሳቸውን ድርሻ ማበርከታቸውን አመልክተዋል፡፡ የልማት ስራውን ለመጀመር የሚያስችሉ የግብርና መሳሪያዎች በዞኑ ለሁሉም ወረዳዎች መቅረቡን ጠቁመዋል፡፡ ዞኑ ቆላማና ዝናብ አጠር እንዲሁም በድርቅ የሚጠቃ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የእንስሳት እርባታ ስራ በስፋት እንደሚካሄድም ተመላክቷል፡፡
በድሬዳዋ የተከናወኑ የተቀናጁ የተፋሰስ ልማቶች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አግዘዋል
Jan 8, 2026 49
ድሬዳዋ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተቀናጁ የተፋሰስ ልማቶች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ማገዛቸውን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። በአስተዳደሩ ባለፉት የለውጥ ዓመታት 56ሺህ ሄክታር የተራቆቱ መሬቶችን በተፋሰሶች በማልማት የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭን ስኬታማ ማድረጉም ተመልክቷል። የፊታችን ጥር 3 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬዳዋ 38 የገጠር ቀበሌዎች የሚጀመረውን የተፋሰስ ልማት አስመልክቶ ለአስተዳደሩ አመራሮችና ነዋሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ የተገኙት ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በድሬዳዋ የተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የጎርፍ አደጋዎችን ከማስቀረት ባለፈ የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭን ስኬታማ አድርገዋል። በተለይም በገጠሩ አካባቢ የተከናወኑ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ተፋሰሶች የአፈር ለምነትን ለመመለስና የገጸ ምድርና ከርሰ ምድር የውሃ ሀብት እንዲጨምር ማድረጋቸውን አንስተዋል። በተጨማሪም የጎርፍ ውሃን ለአነስተኛ መስኖ ልማቶች በማዋል ህብረተሰቡ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ እያስቻሉ ይገኛሉ ብለዋል። ይህን ተሞክሮ በማስቀጠል በዘንድሮው የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት በየደረጃው የሚገኘው አመራርና ህብረተሰቡ በመረባረብ እንዲያሳካም አስገንዝበዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኑረዲን አብደላ በሰጡት መግለጫ፤ በሚቀጥለው እሁድ በ 5 ሺህ 550 ሄክታር የተራቆቱ ተፋሰሶች ላይ የተለያዩ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራዎች እንደሚጀመር ተናግረዋል። በ38ቱ የአስተዳደሩ የገጠር ቀበሌዎች ለአንድ ወር የሚከናወነው የተፋሰስ ልማት ከአፈርና ውሃ ጥበቃ ተግባራት በተጨማሪ ለመጪው ክረምት ለሚተከሉ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኞች ጉድጓዶች ይዘጋጃሉ ብለዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት 56 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተካሄዱት የተፋሰስ ልማቶች የገጠሩን ህብረተሰብ የግብርናና የእንስሳት ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እያሸጋገሩ መሆኑን አንስተዋል። የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ስኬታማ በመሆኑ የማር፣ የወተት፣ የዶሮና የእንቁላል ምርቶችን ማሳደግ ማስቻሉን ጠቅሰው ይህም ህብረተሰቡ ተመጣጣኝ ምግብ እና ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ ማስቻሉን አስረድተዋል። ዘንድሮ ከተፋሰሱ ልማት ጎን ለጎን የገጠሩን ህብረተሰብ በሙሉ የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት የማድረግ ስራ በትኩረት እንደሚሰራ የገለፁት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ኢብራሂም ዩሱፍ ናቸው። አቶ ኢብራሂም አክለው እንዳሉት የገጠሩን ህብረተሰብ የኮሪደር ልማት ባለቤት የማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራም ይከናወናል። ጥር 3 ቀን 2018ዓ.ም በሚጀመረው የተፋሰስ ልማት ስራ ላይ ከ37 ሺህ በላይ አርሶ እና አርብቶ አደሮች እንደሚሳተፉ ተመላክቷል።
በሲዳማ ክልል በዘንድሮው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ከ147 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል
Jan 5, 2026 156
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 27/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በዘንድሮው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ከ147 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ገለፀ፡፡ በክልሉ ከለውጡ ወዲህ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራን ከአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ጋር በማቀናጀት በመሰራቱ ተጨባጭ ለውጦች መመዝገቡ ተመላክቷል። የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራው በተከናወነባቸው አካባቢዎች የተራቆቱ መሬቶችን ወደ አረንጓዴነት መቀየር፣ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር ወደ ቀድሞው መመለስ፣ የአፈር መከላትን መከላከልና የመሬት እርጥበትን በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር እንደተቻለ ተገልጿል፡፡ ምርታማነታቸውን የቀነሱና ምርት መስጠት ያቆሙ ተዳፋት ቦታዎችን በጠረጴዛማ እርከን ሥራ እንዲያገግሙ በማድረግና በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ምርታማነት መቀየር መቻሉም ተጠቅሷል፡፡ በተፋሰስ ልማት ያገገመ መሬት ላይ በሥነ ሕይወታዊ ሥራ የእንስሳት መኖ እንዲሁም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ዕፅዋት በመትከል የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እንዲያድግ መደረጉም ተመላክቷል፡፡ በእስከሁኑ የልማት ሥራ የተገኙ ጥቅሞችን በዘላቂነት ለማሳደግ ዘንድሮም በትኩረት እንደሚሰራ የተናገሩት የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ምክትልና የተፈጥሮ ሀብትና ደን ልማት ዘርፍ ኃላፊ አበባየሁ በየነ ናቸው፡፡ አቶ አበባየሁ ለኢዜአ እንደገለፁት ዘንድሮ በክልሉ በ678 ንዑስ ተፋሰሶች 147ሺህ 335 ሄክታር መሬት በተቀናጀ ሥራ ይለማል። ዘንድሮ ለማልማት የታቀደው ከአምናው አንጻር የስምንት በመቶ ብልጫ እንዳለውና በእነዚህ ቦታዎች የጥናት፣ የዲዛይንና የካርታ ሥራዎች አስቀድሞ መሰራቱን ተናግረዋል። የልማት ሥራውን ለማሳካትም 788 ባለሙያዎች የክህሎት ማጎልበቻ ሥልጠና መውሰዳቸውንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡ በክልሉ የዘንድሮው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ከጥር 1 እስከ 10 ባሉት ቀናት በይፋ ይጀመራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ በቀጣዩ ሳምንት ይጀመራል
Jan 8, 2026 63
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ(PRC) መደበኛ ስብሰባው ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ያተኮረ ነው። በስብሰባው የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብሰባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብሰባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት፤ የአፍሪካ ህብረት የ2026 መሪ ሀሳብ ዋና የትኩረት አጀንዳ
Dec 26, 2025 581
39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ነው። መሪ ሀሳቡን ያረቀቀው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የዘንድሮው መሪ ቃል ከአጀንዳ 2063 ጋር የተቆራኘ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። ሁሉም አፍሪካዊ ንጹህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በቂ ውሃ ለመጠጥ፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና ለሌሎች ፍላጎቶቹ እንዲያገኝ የማድረግ ራዕይን ለማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል። ህብረቱ የውሃ ደህንነት እንደ አህጉር የተያዙ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን በማዕቀፎቹ አስቀምጧል። ውሃ እና ንጽህና የኢኮኖሚ እድሎችን በማስፋት፣ የስራ አጥነት ምጣኔን በመቀነስ፣ የስደቶችና ተፈናቃዮችን ጫና ለማቃለል እንዲሁም ለሰላምና ደህንነት መስፈን አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተመላክቷል። የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ህብረቱ ውሃ እና ንጽህና ለጤና፣ ለኢኮኖሚ እድገት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥና ዘላቂ የአካባቢ ምህዳር ለመፍጠር መሰረት መሆኑን የበለጠ እውቅና እንደተሰጠው አመልክቷል። ሁሉን አቀፍ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይገበር የውሃ ደህንነትን የማረጋገጥ አላማ ካለው የአፍሪካ የውሃ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው። የዘንድሮው መሪ ቃል የአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ጥረቶችን ያስተሳሰረ ድልድይ ሆኗል። በዘላቂ ልማት ግቦች ውስጥ ያለው ግብ ስድስት ከውሃ እና ንጽህና ጋር የተያያዘ ነው። ይህ ግብ እ.አ.አ በ2030 ለሁሌም ዜጋ ደህንነቱ የተረጋገጠ ውሃ አቅርቦትና የንጽህና አጠባበቅን ተደራሽ የማድረግ አላማ አለው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት በፍጥነት መስፋፋትና ውሃ በአግባቡ አለመጠቀም የውሃ ደህንነት እና ዘላቂ አቅርቦት ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። የንጽህና አጠባበቅ የአፍሪካ አንዱ ፈተና ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች መሰረታዊ የሚባል የንጽህና መጠበቂያ መሰረተ ልማቶችን አያገኙም። ይህም እንደ ኮሌራ ላሉ የውሃ ወለድ በሽታዎች መስፋፋት ምክንያት ሆኗል። የተቀናጀ የውሃ አስተዳደር ስርዓት፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ ለዘላቂ መሰረተ ልማት የሚፈሰወን መዋዕለ ንዋይን ማሳደግ፣ ውሃ በድጋሚ አጣርቶ መጠቀም፣ የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ፣ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር እና ለውሃ ደህንነት ትኩረት የሚሰጡ ፖሊሲዎችና ማዕቀፎችን በውጤታማነት መተግበር ያሉትን እድሎች በዘላቂነት ለመፍታትና ፈተናዎችን ለመቅረፍ ያስችላል። ደህንነቱ የተረጋገጠ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ላይ ያለፈውን ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የቆሸሸ ውሃ በአግባቡ ማከም፣ የንጽህና አጠባበቅ ማስፋትና የግንዛቤ ፈጠራ ስራን በስፋት ማከናወን፣ ማህበረሰብ መር የንጽህና አጠባበቅ ኢኒሼቲቮችን ትግበራ ማስፋት፣ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎችና ሀገር በቀል አቅምን መገንባት ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓትን መፍጠር ያስችላል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና ጤናማ ማህበረሰብ ግንባታ ያላቸውን ቁልፍ ሚና የሚያሳይ ነው። የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ማድረግ መሰረታዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ ለማህበረሰብ ደህንነትና የተሻለ የኑሮ ዘይቤ፣ ለአካባቢ ጥበቃና ለአፍሪካ ብልጽግና መረጋገጥ ስትራቴካዊ አቅም ናቸው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በሚካሄድበት ወቅት በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም እና 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኞች ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳሉ። ኢትዮጵያ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የአፍሪካ ጣሊያን ስብሰባን ለማዘጋጀት ብሄራዊ የዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቀን ነው - የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Dec 24, 2025 488
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ሲል የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ገለጸ። የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በኤርትራ መንግሥት አገዛዝ ደረሰብን ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ጋምቢያ(ባንጁል) የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ላቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን አድንቋል። በኤርትራ መንግስት ላይ የቀረቡትን ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክስ ተቀብሎ በመዝገብ ቁጥር 868/25 መመዝገቡን፣ የክሱ ፍሬ ነገር እና ይዘት ተቀባይነት ያለው መሆኑን እውቅና በመስጠት የኤርትራ መንግስት እንዲመልስ ክሱን መላኩን ኮሚሽኑ ማስታወቁን ገልጿል። የድርጅቱ ሊቀ-መንበር ኢብራሂም ሀሩን በመግለጫቸው እንደተናገሩት፤ የኤርትራው መንግሥት በደናክል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ህዝቦች እየፈፀመ ያለው መጠነ ሰፊ፣ ስልታዊ፣ መንግስታዊ መር እና ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በአሁኑ ወቅት እየደረሱ ነው ካሏቸው የመብት ጥሰቶች መካከልም ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ማካሄድ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት፣ በሺዎች የሚቆጠሩትን መሰወር፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ማከናወን መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰው፤ በተለይም ከ300ሺህ በላይ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማፈናቀል እና ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል፣ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋትና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን መጣስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ድርጅቱ የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ከ1993 ጀምሮ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰባቸው ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ክስ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እኤአ ጁን 04 ቀን 2025 በ122 ገጽ የተደራጀ ክስ ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የኤርትራ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን እንደገለጸላቸው ጠቁመዋል። ለክሱም ከተጠቀሙት ማስረጃዎች መካከል በድርጅቱ የተከናወነ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ግኝት፣ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝባዊ መብቶች በኤርትራ ላይ የተደረጉ ምርመራዎች፣ ግኝቶችና ማስረጃዎች፣ የመብት ጥሰት የደረሰባቸው የቀይ ባሕር አፋር ተጎጂ ወገኖች እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የተገኙ የሰብዓዊ መብት ምርመራዎችን መቅረቡን ተናግረዋል። ድርጅቱ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት መከራ ለማዳን፣ የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ድምፅ እንዲሆኑት፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡንና የኢሳያስ መንግስት ላይ ህጋዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጸንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው-ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
Dec 23, 2025 430
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እና ለረጅም ጊዜ ፀንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ኃላፊ አምባሳደር ኮንስታንሲያ አዴሊና ጋስፓራስ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቅርበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት (ዋይት ሃውስ) በተካሄደ ስነ ስርዓት የአምባሳደር ኮንስታንሲያን ሹመት በይፋ ተቀብለዋል። አምባሳደሯ በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ቢሮ ስራቸውን በይፋ ጀምረዋል። ዶናልድ ትራምፕ የአምባሳደር ኮንስታንሲያ የልዑኩ መሪ ሆኖ መመረጥ በጋራ የኢኮኖሚ እድሎች፣ በሉዓላዊ አመራር ሰጪነት እንዲሁም በሰላም እና ደህንነት ላይ የተመሰረተውን የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጽኑ አጋርነት የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በአፍሪካ ሰላም፣ ብልጽግና እና መረጋጋትን ማረጋገጥን ዋና ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የአጋርነት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኝ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 403
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 390
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 612
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 769
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 359
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 340
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 1013
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3355
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 2939
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1865
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7686
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6165
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ብዙ ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን ያቀበሉ ተጫዋቾች
Jan 5, 2026 157
በእግር ኳስ ጨዋታ ከግብ አስቆጣሪዎች ጀርባ ኳስን ፍትፍት አርገው ጨርሰው የሚያቀብሉ ተጫዋቾች አሉ። አንድ ተጫዋች ግብ ሲያገባ ከማግባቱ ባልተናነሰ ማን ኳሱን አቀበለው? የሚለው ጥያቄ በተመልካቾች ይነሳል። በእግር ኳስ እድገት ውስጥ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለጎል ኳስ አመቻችተው የሚያቀብሉ ተጫዋቾች ትልቅ ዋጋ ይሰጣቸዋል። ማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪምን አሰናበተ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች እየተካሄዱ ይገኛሉ። የ33 ዓመቱ የሴኔጋል አምበል ሳዲዮ ማኔ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ካስቆጠረው አንድ ግብ በተጨማሪ ሶስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል የቀዳሚነቱን ስፍራ ይዟል። ማኔ ሴኔጋል ለሩብ ፍጻሜ እንድታልፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ ትልቅ የሚባል ነው። ስምንት ተጫዋቾች በተመሳሳይ ሁለት ለግብ የሚሆኑ ግቦችን አመቻችተው አቀብለዋል። ናይጄሪያውያኑ አዴሞላ ሉክማን እና አሌክስ ኢዎቢ፣ የሞሮኮው አዝዲን ኡናሂ፣ የአልጄሪያው አኒስ ሃጂ-ሙሳ፣ የቡርኪናፋሶው ዳንጎ ኡታራ፣ የቱኒዚያው ሃኒባል ሜጅብሪ፣ የደቡብ አፍሪካው ላይል ፎስተር እና የታንዛንያ ኖቫቱስ ሞሮሺ በሁለት ግቦች ላይ እጃቸው ያለበት ተጫዋቾች ናቸው። የናይጄሪያው የክንፍ የመስመር ተጫዋች አዴሞላ ሉክማን ሁለት ግቦችን በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አስቆጥሯል። የኮትዲቯሩ ክርስቶፈር ኦፔሪ እና የናይጄሪያው ሳሙኤል ቹኩዌዜ በተመሳሳይ አንድ አንድ ግቦች ከመረብ ላይ እንዲቆጠሩ የቀጥታ ተሳትፎ አድርገዋል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬን (ካፍ) የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ኮከብ ተጫዋች ምርጫ ላይ ካስቀመጣቸው መመዘኛ መስፈርቶች አንዱ ማን ብዙ ለጎል የሚሆን አቀበለ? የሚለው ይገኝበታል። 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እስከ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የግብ አግቢዎችና የኳስ አቀባዮቹ ፉክክር በያዘው ግለት ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል።
ወንድማማቾች በአፍሪካ ዋንጫ
Dec 29, 2025 392
የአፍሪካ ዋንጫ መልከ ብዙ ውድድር ነው። የሀገራት ተቀናቃኝነት፣ ታሪካዊ ገድሎች፣ አይረሴ የተጫዋቾች የግል ብቃት፣ ጨዋታ ወሳኝ ግቦች እና ዋንጫን ከፍ አድርጎ የማንሳት የኩራት እና የሀገር ፍቅር ስሜት መገለጫዎቹ ናቸው። ከሚቆጠሩ ግቦች እና ዋንጫዎች ባለፈ ቤተሰባዊ ገጽታ ያለው ነው። የአፍሪካ ዋንጫ በርካታ ወንድማማች ተጫዋቾች በአንድ ሀገር ማልያ ሲጫወቱ የተመለከትንባቸው አጋጣሚዎች በርካታ ናቸው። በአህጉራዊው መድረክ የ68 ዓመታት ጉዞ አብረው የተጫወቱ ወንድማቾች በዚሁ ጽሁፍ እንመለከታለን። 1. ኢታሎ እና ሉቺያኖ ቫሳሎ (ኢትዮጵያ) ኢታሎ ቫሳሎ እና ሉቺያኖ ቫሳሎ በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጫወቱ ወንድማማቾች መሆናቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1962 ባዘጋጀችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የቫሳሎ ወንድማማቾች አንድ ላይ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጫውተዋል። ሉቺያኖ በውድድሩ ላይ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ከግብጹ ባደዊ አብድል ፈታህ ጋር በጋራ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ አጠናቋል። ሉቺያኖ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ተብሎ የተመረጠ ሲሆን ይህም በውድድሩ ታሪክ የኮከብ ተጫዋችነትን ሽልማት ያገኘ የመጀመሪያው ተጫዋች እንዲሆን አስችሎታል። ኢትዮጵያ በወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳቷ የሚታወስ ነው። 2. ሆሳም እና ኢብራሂም ሀሰን (ግብጽ) ሆሳም ሀሰን እና ኢብራሂም ሀሰን በአፍሪካ ዋንጫው ስኬታማ የሚባሉ ወንድማማች ተጫዋቾች ናቸው። እ.አ.አ በ1986 ግብጽ ያስተናገደችውን 15ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና እ.አ.አ በ1998 በቡርኪናፋሶ የተካሄደውን 21ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ግብጽ ስታነሳ የቡድኑ አባላት ነበሩ። ወንድማማቾቹ የአፍሪካ ዋንጫን ሁለት ጊዜ በማንሳት ባለ ክብረ ወሰን ናቸው። የ59 ዓመቱ ሆሳም ሀሰን በአሁኑ ሰዓት የግብጽ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነው። በተጫዋችነቱ በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የምንጊዜውም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። 3. አልበርት ባዋንጋ እና ሮበርት ካዛዲ (ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ) ሁለቱ ወንድማማቾች ግብጽ እ.አ.አ በ1974 ባዘጋጀችው ዘጠነኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። በወቅቱ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ዛምቢያን በማሸነፍ ዋንጫውን ስታነሳ የታሪካዊው ድል አካል ነበሩ። 4. አንድሬ ካና ቢይክ እና ፍራንስዋ ኦማም ቢይክ (ካሜሮን) ሁለቱ ወንድማማቾች በሶስት የአፍሪካ ውድድሮች ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። ተጨዋቾቹ ለመጀመሪያ ጊዜ በአህጉራዊ መድረክ በጋራ የመሰለፍ እድል ያገኙት እ.አ.አ በ1988 በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው 16ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። እ.አ.አ በ1990 በአልጄሪያ በተካሄደው 17ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ሴኔጋል እ.አ.አ በ1992 ባዘጋጀችው 18ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። ጣልያን እ.አ.አ በ1990 ባዘጋጀችው 14ኛው የዓለም ዋንጫ ከወንድማማቾቹ ታናሹ ፍራንስዋ ኦማም ቢይክ ካሜሮን አርጀንቲናን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ባስቆጠራት ጎል ሁሌም በሀገሬው ሰዎች ሲወሳ ይኖራል። 5. አንድሬ አየው እና ጆርዳን አየው (ጋና) ጋናውያኑ ወንድማሞች የአፍሪካ ዋንጫ ሲነሳ ሁሌም የሚታወሱ ተጫዋቾች ናቸው። በስድስት የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ አብረው ተሰልፈዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ አብረው የሰለፉት ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን እ.አ.አ በ2012 ባዘጋጁት 28ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነው። የአየው ወንድማማቾች እ.አ.አ በ2015 ኢኳቶሪያል ጊኒ ባዘጋጀችው 30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማንሳት ተቃርበው የነበሩ ቢሆንም በፍጻሜው በኮትዲቭዋር በመለያ ምት ተሸንፈው ህልማቸው ሳይሳካ ቀርቷል። የታዋቂው አፍሪካዊ ተጫዋች አብዲ ፔሌ ልጆች የሆኑት አንድሬ እና ጆርዳን አየው እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለመጨረሻ ጊዜ በጋራ ተሰልፈዋል። ጋና እ.አ.አ በ2008 ባዘጋጀችው 26ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ጋናዊው አጥቂ አሳሞሃ ጊያን እና ታናሽ ወንድሙ ባፎር አንድ ላይ ተጫውተዋል። በተጨማሪም በዛው ውድድር ላይ ጋናውያኑ ወንድማማቾች ሪቻርድ ኪንግስተን እና ላሪያ ጊንግስተን አብረው የመጫወት እድል አግኝተዋል። 6. ኮሎ ቱሬ እና ያያ ቱሬ (ኮትዲቭዋር) በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ስማቸው በግንባር ቀደምትነት ከሚነሱ ተጫዋቾች መካከል ኮሎ ቱሬ እና ያያ ቱሬ ይጠቀሳሉ። ወንድማማቾቹ ለመጀመሪያ ጊዜ አብረው የተሰለፉት እ.አ.አ በ2006 በግብጽ አስተናጋጅነት በተካሄደው 25ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነው። በወቅቱ ኮትዲቭዋር ለፍጻሜ ደርሳ በግብጽ ተሸንፋለች። ኢኳቶሪያል ጊኒ እ.አ.አ በ2015 ባዘጋጀችው 30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኮትዲቭዋር ጋናን በማሸነፍ ዋንጫውን ለሁለተኛ ጊዜ ስታነሳ በጋራ የድሉ ተቋዳሽ ሆነዋል። የቱሬ ወንድማማቾች ለስድስት ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫው አብረው ተጫውተዋል። 7. የሞሪታኒያ እና ዛምቢያ ወንድማማች ተጫዋቾች እ.አ.አ በ2023 ኮትዲቭዋር ባስተናገደችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሪታኒያ ብሄራዊ ቡድን ስብስብ ከሁለት ቤተሰብ በተመሳሳይ ሁለት ወንድማማቾች መሳተፋቸው የተለየ ትኩረት ስቧል። ኑህ መሐመድ አብድ እና ታናሹ ሲዲ መሐመድ አህመድ አብድ በተከላካይ እና አማካይ መስመር ላይ ተሰልፈው ተጫውተዋል። ላሚን ባ እና ኤል ሃጂ ባ ለሞሪታኒያ ብሄራዊ ቡድን በመሰለፍ መጫወት ችለዋል። ዛምቢያዊያኑ ክርስቶፈር እና ፍሊክስ ካቶንጎ እ.አ.አ በ2012 ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን በጣምራ ባዘጋጁት 28ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ዛምቢያ ኮትዲቭዋር በማሸነፍ የአፍሪካ ዋንጫን ስታነሳ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2013 ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይም በጋራ ተሰልፈው ተጫውተዋል። ዛምቢያውያኑ ወንድማማቾች ኬኔት እና ሞርዶን ማሊቶሊ እ.አ.አ በ1994 በቱኒዚያ በተካሄደው 19ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ1996 ባዘጋጀችው 20ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አንድ ላይ ተሰልፈዋል። አለን ትራኦሬ እና ኢብራሂማ ትራኦሬ (ቡርኪናፋሶ) በ30ኛው እና 31ኛው የአፍሪካ ፣ ሳምቡ ያታባሬ እና ሙስጠፋ ያታባሬ (ማሊ) በተመሳሳይ በ30ኛው እና 31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ፒተር ንዶልቩ እና አዳም ንዶልቩ (ዚምባቡዌ) በ24ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ሳሉ፣ ባቺሩ እና ታጁ (ቶጎ) በ22ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ቾሞጎ ኦማር እና ሴዲያት ኦማር (ቤኒን) በ24ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ መሐመድ እና ሙሳ ካሎን (ሴራሊዮን) በ20ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ሳሚር ሳሊሚና አዴል ሳሊሚ (ቱኒዚያ) በ19ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አብረው የተሰለፉ ተጫዋቾች ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫ ከተሰለፉ ወንድማማቾች መካከል ስድስቱ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳታቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስታውቋል።