ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የከተማውን ሰላምና ልማት በማስጠበቅ ረገድ የንግዱ ማህበረሰብ እያበረከተ ያለውን ሚና እንዲያጠናክር ተጠየቀ
Mar 6, 2026 10
ባህር ዳር፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፡- የባህር ዳር ከተማን ሰላምና ልማት በማስጠበቅ ረገድ የንግዱ ማህበረሰብ እያበረከተ ያለውን ሚና የበለጠ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው የከተማ አስተዳደሩ አስገንዝቧል። የከተማ አስተዳደሩ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በከተማዋ ከሚገኙ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አካሄዷል። በውይይት መድረኩ ላይም የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ እንዳሉት የከተማውን ሰላምና ልማት በማስጠበቅ ረገድ የንግዱ ማህበረሰብ እያበረከተ ያለውን ሚና አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። በከተማዋ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች ሰፋፊ የህዝብን ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ የሚችሉ የልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑና እየተፋጠኑ መሆኑን ገልጸዋል። የንግድ ማህበረሰብም በከተማዋ እየተከናወኑ ባሉ የኮሪደርም ሆነ ሌሎች የልማት ስራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑን አውስተዋል። በክልሉ አሁን ላይ የሰፈነውን ሰላም በማፅናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የንግዱ ማህበረሰብ የተጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል። በመሆኑም ለከተማዋ ሰላምና ልማት መረጋገጥ እያበረከተ የሚገኘውን አስተዋፅኦ አጠናክሮ ሊያስቀጥል እንደሚገባም ምክትል ከንቲባው አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ጌጡ አንዳርጌ እንደገለጹት፤ የከተማውን ሰላምና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ነጋዴው ማህበረሰብ በተደራጀ አግባብ እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል። ሌላኛዋ ተሳታፊ ወይዘሮ ዋጋ አዘዘ በበኩላቸው በከተማዋ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ እየተደረገ ባለው ጥረት እየተወጣን የምንገኘውን ሚና እናጠናክራለን ብለዋል። በመድረኩ በከተማው በተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ ነጋዴዎችና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።
በዞኑ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል ይደረጋል
Mar 6, 2026 36
አምቦ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሸዋ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች የበለጠ ውጤታማ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉ በዞኑ ምልከታ ያደረጉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የጨፌ ኦሮሚያ አባላት ተናገሩ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የጨፌ ኦሮሚያ አባላት በዞኑ በቶኬ ኩታዬ፣ በኢሉ ገላን እና በባኮ ወረዳዎች በኩታ ገጠም የለማ የሙዝ፣ የፓፓያ፣ የበጋ ስንዴና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። አባላቱ ከጉብኝቱ በኋላ በዞኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት እንዲጠናከሩ የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የዳኖ ምርጫ ክልል ተወካይ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር)፤ በዞኑ እየተከናወኑ ከሚገኙ የልማት ስራዎች በተለይም በግብርናና በሌሎች ልማቶች ላይ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሥራዎቹ በቴክኖሎጂ እንዲደገፉና አስፈላጊ ግብዓቶች እንዲሟሉላቸው ድጋፍ እና ክትትል በማድረግ የሀገሪቱን እድገት በማፋጠን ረገድ የራሳቸውን ድርሻ እንደሚወጡም ተናግረዋል። ሌላዋ የጨፌ ኦሮሚያ አባልና የባኮ ምርጫ ክልል ተወካይ ወይዘሮ ኤቢሴ ፍርዲሳ በበኩላቸው፤ በዞኑ ከዚህ ቀደም ተሰርተው የማያውቁ ትላልቅ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውንና ለሕብረተሰቡ የሥራ ዕድል መፈጠሩን መታዘባቸውን ገልጸው፣ ይህም የሀገሪቱን እድገት እንደሚያፋጥን ተናግረዋል። በተጨማሪም የሕዝብና የመንግሥት ሀብት ከሌብነትና ከብክነት በጸዳ መልኩ ለልማት እንዲውል አስፈላጊውን ክትትል እንደሚያደርጉና ሁሉም በዚህ ላይ እንዲሳተፍ መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የጨፌ ኦሮሚያ አባላት ባደረጉት ጉብኝት ለሰጡት ገንቢ አስተያየት ያመሰገኑት የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አበበ ጨመዳ ናቸው። የቀረቡትን ገንቢ ሐሳቦች በመጠቀም በዞኑ ከዚህ በላይ ያሉ የልማት ሥራዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በጥራትና በትኩረት ለመሥራት መታቀዱን ገልጸዋል። በዞኑ የተሰሩ የልማት ሥራዎች አበረታች ቢሆኑም፣ ከዚህ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከሕብረተሰቡ እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ይጠናከራሉ ብለዋል። በልማት ስራዎች የመስክ ምልከታው ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የጨፌ ኦሮሚያ አባላትን ጨምሮ የዞኑ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
በክልሉ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የኃይማኖት አባቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል-ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Mar 6, 2026 34
ባሀርዳር፤የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በስነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ በመገንባት ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የኃይማኖት አባቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለፁ። "የመደመር መንግስት እና የኃይማኖት ተቋማት ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ ከወንጌላዊያን፣ ካቶሊክና ከ7ኛ ቀን አድቬንቲስት የሃይማኖት መሪዎች ጋር ክልላዊ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው። ርዕሰ መስተዳደሩ አቶ አረጋ ከበደ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፤ የኃይማኖት አባቶች የተረጋጋ ሀገረ መንግስት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ሚናቸው ከፍተኛ ነው። በተለይም ለተከታዮቻቸው ሰላምን በመስበክ፣ ትውልዱን በስነ-ምግባር በማነፅና በመገንባት ያላቸውን ሚና በተሻለ መንገድ መወጣት እንደሚገባቸው ነው የተናገሩት። ኢትዮጵያ የብዝሃ ኃይማኖትና ቋንቋዎች ሀገር በመሆኗ ይህንን ጸጋ ለላቀ የሀገር ግንባታ ለማዋል በጋራ መስራት አሰፈላጊ በመሆኑ የውይይት መድረኩ መዘጋጀቱን ገልፀዋል። የኃይማኖት አባቶች በክልሉ የሚስተዋሉ የሰላም ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራትም የተሻለ አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው ያመለከቱት። የኃይማኖት አባቶች እስካሁን ለመጣው ሰላምና ልማት የጎላ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን ጠቁመው በቀጣይም ይህንኑ አጠናክረው መቀጠል እንደሚጠበቅባቸው ነው ያሳሰቡት። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኃይማኖት አባቶች ለሀገረ መንግስት ግንባታ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ለሀገር ሰላምና ለትውልድ ግንባታ አበርክቷቸው ከፍተኛ በመሆኑም ሰላምን ለማጽናት በሚደረገው ጥረት ድርሻቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል። በተለይም ገዥ ትርክት ላይ የተመሰረተ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለመገንባት መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት ስኬታማ እንዲሆንም ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። በሀገራዊና ህዝባዊ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የዕምነት አባቶችና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
አርሶ አደሩ በበልግ ወቅት የሚጠበቀውን የዝናብ ስርጭት ተጠቅሞ የሰብል ምርታማነቱን ማሳደግ አለበት
Mar 6, 2026 41
ደሴ ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦አርሶ አደሩ በበልግ ወቅት የሚጠበቀውን መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ተጠቅሞ የሰብል ምርታማነቱን ማሳደግ እንዳለበት በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምስራቅ አማራ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አስታወቀ። በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ ነው የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ በበኩሉ ከ104 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበልግ ዝናብ ለማልማት መታቀዱን አስታወቋል። በማዕከሉ የትንበያና ቅደመ ማስጠንቀቂያ ዴስክ ኃላፊ ወይዘሮ ሉባባ መሀመድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በልግ ለምስራቅ አማራ ቀጠና ከመኸር ቀጥሎ 2ኛው የምርት ወቅት ነው። ከተያዘው ወር መጨረሻ ጀምሮ ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ወሎ እና ሰሜን ሸዋ ዞኖችን ጨምሮ ምስራቅ አማራ ቀጠና መደበኛና ከመደበኛ በላይ የበልግ ዝናብ ይጠበቃል ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም በደቡብ ወሎ እና በሰሜን ወሎ ዞን ዝናብ መጣል መጀመሩን ጠቁመው፣ አርሶ አደሩ በበልግ የሚጥለውን ዝናብ በመጠቀም የዘር ሥራውን አጠናከሮ ማስቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። ለዚህም የበልግ ዝናብን በማሳው ዳርና ውስጥ ላይ በማቆር በደረቅ ወቅት ለመጠቀም የሚያስችል ዝግጅት እንዲያደርግም መክረዋል። እንደሃላፊዋ ገለጻ ፤የበልግ ዝናብ ለሰብል ልማት፣ የአፈር እርጥበትን ለማሻሻል፣ ለእንስሳት ግጦሽ፣ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። ቅጽበታዊ ጎርፍ፣ የሰብል በሽታና ተባይ ተከስቶ ጉዳት እንዳይደርስ አርሶ አደሩ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበትም አሳሰበዋል። በደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ በበኩላቸው፤በዞኑ በበልግ ወቅት ከ104 ሺህ 600 ሄክታር በላይ መሬት በተለያየ ሰብል እንደሚለማ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የበልግ ዝናብ በአካባቢው መዝነብ መጀመሩን ገልጸው፣ አርሶ አደሩም የዘር ሥራውን አጠናክሮ በማስቀጠል ምርታማነቱን እንዲያሳድግ እየተሰራ ነው ብለዋል። በበልግ እርሻ ምርታማነትን ለማሳደግም ለአርሶ አደሩ ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያና ሌሎች ግብአቶችን የማቅረብ ሥራ መሰራቱን አመልክተዋል፡፡ በበልግ ልማት እየተሳተፉ ካሉ የደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር ኢብራሂም በሽር፤ አንድ ሄክታር ማሳቸውን በበልግ ለማልማት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በእስካሁኑ የልማት ሥራም ለበልግ ያዘጋጁትን የተፈጥሮ ማዳበሪያ አለስልሰው ባዘጋጁት ማሳ መበተናቸውን ገልጸው፣ በመንግስት ሰው ሰራሽ ማዳበሪያም እንደቀረበላቸው ተናግረዋል። በዚሁ ዞን የለጋምቦ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ይማም አሊ በበኩላቸው፤ አንድ ሄክታር ተኩል ማሳቸው ላይ በበልግ ስንዴ፣ ገብስና ምስር ለማልማት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ልደታ ክፍለ ከተማ እና ቦሌ ክፍለ ከተማ ነጥብ ተጋሩ
Mar 6, 2026 34
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ልደታ ክፍለ ከተማ እና ቦሌ ክፍለ ከተማ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። በኤፍኤ ካፕ ሊቨርፑል ከዎልቭስ ጋር ይጫወታል በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሰብለወንጌል ወዳጆ እና ይታገሱ ተገኝወርቅ ለልደታ ክፍለ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ቃልኪዳን ሸዋነህ እና ዳሳሽ ሰውአገኝ የቦሌ ክፍለ ከተማን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። የልደታ ክፍለ ከተማዋ ሜሮን አበበ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። ውጤቱን ተከትሎ ልደታ ክፍለ ከተማ በ15 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ቦሌ ክፍለ ከተማ በ30 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ፖለቲካ
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ዝግጁ ነን - የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 54
መቱ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ዘንድሮ በሚካሄደው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን በኦሮሚያ ክልል የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ። ካርድ ወስደን በመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል -የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም የሚካሔደው ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ እየሰራ ይገኛል። ከዝግጅቶቹ መካከል ከነገ የካቲት 28/2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሔደው የመራጮች ምዝገባ ተጠቃሽ ነው። ቦርዱ በአጠቃላይ ከሚኖሩት የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17ሺህ ያህሉ የዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቦር ዞን የሁሩሙ ወረዳ ነዋሪዋ ህዝባለም ደገፉ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ መብቴን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ እየተጠባበኩ ነው ብለዋል። የመቱ ወረዳ ነዋሪዋ ዝማርጉ ጀማል እና ናሐዊ ደፋር በበኩላቸው፤ በመራጭነት ተመዝግበው መብታቸውን ለመጠቀም እንዲችሉ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ምርጫ ለሀገረ መግሥት ግንባታ ወሳኝ ምእራፍ በመሆኑ የዜግነት ግዴታዬን በኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ ነኝ የሚለው ደግሞ የመቱ ከተማ ነዋሪው ወጣት በፈቃዱ እንዳለ ነው። ወጣት ፌዴሳ ታረቀኝ እና ግርማ ፍሪሳ በበኩላቸው፤ ጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እንደ ወጣት የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል። በሀገረ መንግስት ግንባታ ውስጥ ሴቶችና ወጣቶች የሚኖራቸው ሚና የላቀ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ በመውሰድ የሚወክለንን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። በተለይም በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚውና በማህበራዊ ዘርፎች ዘላቂ ተጠቃሚነታችን የሚያረጋግጥልን ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት የመራጮች ምዝገባ እስኪጀመር እየጠበቅን ነው ብለዋል።
የጥፋት ቡድኑን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን - የትግራይ ተወላጆች
Mar 6, 2026 99
ሐረር/አሶሳ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለጥፋት የቆመውን የህወሓት ቡድን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በሐረር እና በአሶሳ ከተሞች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ። የትግራይ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሰሞኑን በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ እንደሆነ ጠቁመው የሰላም እና ልማት ፍላጎቱ ትልቅ መሆኑን ገልጸዋል። በሁሉም ክልሎች እየመጣ ያለው ልማትና ሰላም የትግራይ ህዝብም ይገባዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአረጀ አስተሳሰብ ለዳግም ጦርነትና ውድመት የሚጥረው የሕወሓት ቡድን ተው ሊባል ይገባል ማለታቸው ይታወሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ በሐረር እና በአሶሳ ከተሞች ኢዜአ ያነጋገራቸው የትግራይ ተወላጆች፤ የህወሓት ቡድን ከጥፋትና የጦርነት እቅድ በስተቀር ለህዝብ ሰላምና ልማት መስራት የማይፈልግ ስብስብ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቡድኑን እኩይ ዓላማ እና የህዝቡን የሰላምና የልማት ፍላጎት በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ ተክክለኛ እና ወቅታዊ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ በመደገፍ ለጥፋት የቆመውን ቡድን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን ነው ያሉት። በሐረር ከተማ የሚኖሩት ወይዘሮ ጊዮርጊስ ሃጎስ፤ የጥፋት ቡድኑ መቼም ቢሆን ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ልማት ሰርቶ የማያውቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት ከማይሻው የሻዕቢያ መንግስት ጋር ግንባር በመፍጠር አካባቢውን የጦርነት ቀጣና ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸው ይህንን እኩይ ዓላማ በፅኑ እንታገለዋለን ብለዋል። የአሶሳ ከተማ ነዋሪው ጎይቶም በየነ፤ የህወሓት የጥፋት ቡድን እሳቤ ጊዜው ያለፈበትና ለማንም የማይጠቅም መሆኑንና የትግራይ ህዝብ አሁን ላይ እንደሌሎች ክልሎች በአዲስ እሳቤና በአዲስ ትውልድ መመራትን አጥብቆ ይሻል ብለዋል። በመሆኑም የህወሓትን ቡድን ጊዜው ያለፈበት አስተሳሰብ በጋራ በመታገል ለክልሉ ሰላም፣ ልማትና ተጠቃሚነት በተባበረ አቅም እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። በሐረር ከተማ የሚኖረው ሼኖክ ሊላይ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ያስተላለፉት መልእክት ለሀገር ሰላምና ልማት የሚጠቅም በመሆኑ ሁላችንም የምንደግፈው ነው ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደ ሌሎች ክልሎች ሁሉ ለትግራይ ክልል ህዝብ ሰላም፣ ልማትና እድገት ያስፈልገዋል ማለታቸው ተገቢ መሆኑን አንስቶ ለዚህም በተለይም የክልሉ ተወላጆች የበኩላችንን እንወጣለን ሲል ተናግሯል። ሌላኛው በአሶሳ ከተማ የሚኖረው ወጣት ክብሮም ገብረመድህን፤ በኢትዮጵያ ከመጣው ለውጥና ሁለንተናዊ የልማት እቅዶች ተጠቃሚ ለመሆን የትግራይ ህዝብ አጥብቆ ይሻል ሲል ገልጿል። ይህንን እውን ለማድረግ ደግሞ ለግጭትና ጦርነት እየሰራ የሚገኘውን የህወሓት የጥፋት ስብስብን በጋራ መታገል ሲቻል ብቻ መሆኑን ገልፆ ለዚህም በተለይ ወጣቶች አደራችንን ለመወጣት እንሰራለን ብሏል። በሐረር ከተማ ያገኘናቸው ወጣት ሳሙኤል መለስ እና ወጣት ፍሬህይወት ብርሃነ፤ የትግራይ ወጣቶች አሁን ላይ የህወሓትን የጦርነት ነጋሪት ሸሽተው እየተሰደዱ መሆኑን አንስተው ነገር ግን ስደት መፍትሄ የማያመጣ በመሆኑ ለትግራይ ህዝብ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና ለውጥ እንዲመጣ በትብብር እንሰራለን ብለዋል።
ካርድ ወስደን በመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል -የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 120
ሚዛን አማን፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለምርጫው ካርድ በመውሰድ ይበጀናል የሚሉትን የመምረጥ ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሂደት ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተሻለ ሀሳብ ያለው ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - ነዋሪዎች ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች፤ ለምርጫው ካርድ በመውሰድ ይበጀናል የሚሉትን አካል የመምረጥ ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ይረፉ መሸሻ ፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም የሚሰራ ፓርቲን ለመምረጥ ከወዲሁ ዝግጅት እያደረግን ነው ብለዋል። በምርጫው በመሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እንደሚወስዱም ገልጸዋል፡፡ ወይዘሮ ሶስና ሀብተማርያም የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ በበኩላቸው፤ በምርጫ መሳተፍ ሕገ መንግስቱ የሰጠን ዲሞክራሲያዊ መብት መሆኑን በመረዳት እየተዘጋጀን ነው ብለዋል። የሚወክለኝን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሐ ግብር መሠረት ተመዝግቤ ካርድ ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ ነው ያሉት። የሀገረ መንግሥት ግንባታን የማጠናከር አንዱ አካል የሆነው የምርጫ ሥርዓት ላይ መሳተፍ ከአንድ ዜጋ የሚጠበቅ ኃላፊነት ነው ያለው ደግሞ ወጣት መልካሙ አሰፋ ነው። ከሕዝብ ጋር ሆኖ የተሻለች ኢትዮጵያን ይፈጥራል የሚለውን ፓርቲ ለመምረጥ በሀሳብ ላይ የተመሠረተ ዝግጅት ማድረጉን ተናግሯል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ አለማየሁ ሻርንስ ምርጫ ዜጎች የሀገራቸው የነገ ዕጣ ፈንታ ላይ የሚወስኑበት ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት የሚመሠረተው በምርጫና ምርጫ ብቻ በመሆኑ ለአካባቢ ልማትና ዕድገት የተሻለ አማራጭ ይዞ የሚመጣን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል። ኢዜአ ተዘዋውሮ እንደተመለከተው ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሚዛን ተፈሪ ምርጫ ክልል በተለያዩ ቀጠናዎች የምርጫ ጣቢያ የማደራጀት ሥራ ተከናውኗል።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተሻለ ሀሳብ ያለው ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 93
ጅግጅጋ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለሀገሪቱ ዕድገትና ለህዝቦች ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጀምር ማስታወቁ ይታወሳል ለመራጭነት የሚያበቃንን ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች፤ በመጪው ግንቦት 24 በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚችሉበትን ካርድ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝብና ለሀገር ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም አስታውቀዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ጀማል ኢብራሂም፤ በአምስት ዓመት አንዴ የሚካሄደው ምርጫ ዜጎች ለሀገርና ህዝብ ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ የሚመርጡበትን ዕድል የሚያመቻች መሆኑን ተናግረዋል። በሶማሌ ክልል በአሁኑ ወቅት ያለው ሠላምና ፀጥታ ከዚህ ቀደም ከነበሩ ምርጫዎች በተሻለ መልኩ ለመሳተፍና ድምጽ ለመስጠት ሰፊ ዕድል መፍጠሩን ገልጸው፤ ይህንን ተጠቅመው በንቃት እንደሚሳተፉም አረጋግጠዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ መሀመድ ዑመር በበኩላቸው፤ ጠቅላላ ምርጫው የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማፋጠንና ለሀገር ዕድገት የሚረዳ ወሳኝ ሥርዓት መሆኑን ገልጸዋል። ለሀገር ይጠቅማል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል። በጠቅላላ ምርጫው ለመራጭነት የደረሱ ዜጎች በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸውም አክለዋል። ምርጫ የአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መገለጫ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ፈርሃን ሙሀመድ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። ካርድ በመውሰድ ለሀገር ዕድገት ይሰራል፤ የዜጎችን ህይወት ይለውጣል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙ ተናግረዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ለመራጭነት የሚያበቃንን ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል
Mar 6, 2026 78
ሀዋሳ/ቦንጋ/ሰመራ/አምቦ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ አካባቢ ነዋሪዎች ገለጹ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ የጊዜ ሰሌዳዎችን ከማስቀመጥ ጀምሮ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እያከናወነ ነው። ከነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የመራጮች ምዝገባ የሚጀመር በመሆኑም ኢዜአ የመራጮችን ዝግጅትን አስመልክቶ በተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎችን አነጋግሯል። የቦንጋ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ነስረዲን ሀሰን፤ በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሔደው ምርጫ ተመዝግበው ካርድ ለመውሰድና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም እየተጠባበቁ መሆኑን ገልፀዋል። ''በግሌም ይሁን ለአካባቢያችን እና ለሀገር የሚበጅ ፓርቲ በመምረጥ ሂደት የእኔ ድምፅ ዋጋ እንዳለው ስለምረዳ ለመምረጥ የሚያበቃኝን ካርድ ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ'' ነው ያሉት። የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ እናኑ ከተማ፤ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚዲያ ስለፕሮግራማቸው የሚያስተላልፉትን ሀሳብ በመከታተል ይበጀኛል ያሉትን ለመምረጥ ከወዲሁ እየተዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል። በምርጫው ለመሳተፍ ዝግጁ ሆነው በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን የተናገሩት ወይዘሮ እናኑ ለእኔም ሆነ ለሀገር ይበጃል የምለውን ፓርቲ እመርጣለሁ ብለዋል፡፡ በዘንድሮው ምርጫ በድምጻቸው የሚበጃቸውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የመራጮች ምዝገባ ቀንን እየተጠባበቁ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሠመራ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ሐዋ አብዱ ናቸው። በተለይም ሴቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በመራጭነት በመሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸውም አስረድተዋል። በምዕራብ ሸዋ ዞን የቶኬ ኩታዬ ወረዳ ነዋሪ ወጣት ቢንያም አሸቱ፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ካርድ ለመውሰድ የምዝገባውን መጀመር እየተጠባበቀ መሆኑን ነው የተናገረው።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል
Mar 6, 2026 126
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ የምርጫ ካርዳቸውን በወቅቱ በመያዝ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ወጣቶች እና ሴቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፣ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ዴሞክራሲያዊና በቴክኖሎጂ የታገዘ ሆኖ እንዲካሄድ በርካታ አስቻይ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል በዚህም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች አስፈላጊ የምርጫ ቅድመ ዝግጅት ስራዎችንም እየተከናወኑ ይገኛሉ። በተጨማሪም፣ በቦርዱ መርሀ ግብር መሠረት የመራጮች ምዝገባ ሂደት ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ይጀመራል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች እና ሴቶች ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት እየተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ወጣት ማርቆስ እሸቱ ከዚህ ቀደም በተካሄዱ ምርጫዎች ላይ በመሳተፍ እንደ ዜጋ ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የሚጠበቅበትን መወጣቱን ተናግሯል። ዘንድሮ የሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ካለፉት ጊዜያት በተሻለ የሚጠበቅበትን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ነው የተናገረው። ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ዘሀራ በርጋ፤ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግና የምሰጠው ድምጽ ዋጋ እንደሚኖረው በማወቅ ይበጀኛል የምለውን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብላለች። በተለይም ሁሉም ወጣት ይበጀኛል ወይም ተጠቃሚነቴን ያረጋግጥልኛል የሚለውን ፓርቲ መምረጥ እንዳለበት ገልጻለች፡፡ ወጣት አህመድ አሊ በበኩሉ፤ ወጣቱ ምርጫ ለአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ዕድገት ያለውን ጉልህ ፋይዳ በሚገባ ሊገነዘብ እንደሚገባ አንስቷል። የዴሞክራሲ ባህላችን ሊያድግ የሚችለው በወጣቶች ተሳትፎ ነው ሲልም ጨምሮ ተናግሯል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ የውብዳር ተመስገን፤ ምርጫ ተጠቃሚነትታችንን የምናረጋግጥበት መንገድ በመሆኑ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብላለች። መምረጥ ሕገ-መንግስታዊ መብት መሆኑን በመጥቀስ፣ ይህንን ዕድል በመጠቀም ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ የበኩሉን ሚና እንደሚወጣ የገለፀው ደግሞ ወጣት ዮሴፍ አበራ ነው። የመምረጥ መብቱን ለማረጋገጥም የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ሀላፊ ሙህዲን ናስር ፌዴሬሽኑ ቀደም ባሉት ምርጫዎች ወጣቱን በማንቃት ረገድ አዎንታዊ አስተዋፅኦ ማበርከቱን አስታውሰዋል። ዘንድሮ የሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን በተለይም ወጣቶችና ሴቶች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በተለያዩ አማራጮች ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
የአካባቢያችንን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የልማት ተሳትፏችንን እናጠናክራለን
Mar 5, 2026 145
ወልዲያና ባህር ዳር ፤ የካቲት 26/2018(ኢዜአ)፦ የአካባቢያችንን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የልማት ተሳትፏችንን እናጠናክራለን ሲሉ የባህር ዳር እና ወልዲያ ከተሞች የመንግስት ሰራተኞች ገለጹ። የተጀመሩ የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ የድርሻችንን እንወጣለን- የሐይማኖት አባቶችና የመንግስት ሰራተኞች የወልዲያና የባህር ዳር ከተሞች አስተዳደሮች የመንግስት ሰራተኞች "ለሰላም ዘብ እንቆማለን፤ የልማት አርበኛም እንሆናለን" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ውይይት አካሄደዋል። በወልዲያ ከተማ በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ የተሳተፉት አቶ አሳዬ በላይነህ እንደገለጹት፤ ጸረ ሰላም ሀይሎችን በመመከት ድርሻቸውን ለማጠናከር ተዘጋጅተዋል። የአካባቢን ሰላም በዘላቂነት በማረጋገጥ የአገርን እድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግ ሁሉም ዜጋ በየተሰማራበት የሥራ መስክ መትጋት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ፈንታው አዲሱ በበኩላቸው አገራቸውን ክደው ከጠላት ጋር የሚያብሩ ኃይሎች ከባንዳነት ያለፈ ታሪካዊ ጠላቶች ናቸው ብለዋል። በአካባቢያቸው ሰላም እንዲሰፍን እና ልማት እንዲፋጠን በአንድነት መቆም እንደሚገባም አመልክተዋል። በብልጽግና ፓርቲ የወልዲያ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ገብሬ፤ የውስጥ ባንዳዎችንና የውጭ ጠላቶችን ሴራ በመመከት አገርን ከነክብሯ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል። ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የመንግስት ሰራተኛው የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል። በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው ውይይት ላይ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ግዛቸው፤ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን ገልፀዋል። የመንግስት ሰራተኛው ሰላምን አፅንቶ ማስቀጠልና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እንዲሁም የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የሚሰሩ ስራዎች ውስጥ እየተወጣ ያለውን ሚና ማጠናከር አለበት ብለዋል። በተጨማሪም የመንግስት ሰራተኛው በሰዓቱ በመገኘትና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህዝብ ቅሬታዎችን ማስወገድ እንዳለበት አመልክተዋል። በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አሁን ያለውን ሰላም አፅንቶ ማስቀጠል እንደሚገባም አሳስበዋል።
የትግራይ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል
Mar 5, 2026 106
አሶሳ/አዳማ/ሶዶ፤ የካቲት 26/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ክልል ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቀናት በፊት ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ መሆኑን አንስተው የሰላም እና ልማት ፍላጎቱ ትልቅ መሆኑንም ገልጸዋል። የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤን የማስቀጠል አባዜ ምክንያት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሁሉም ክልሎች እየመጣ ያለው ልማትና ሰላም የትግራይ ህዝብም ይገባዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአረጀ አስተሳሰብ ለዳግም ጦርነትና ውድመት የሚጥረው የህወሃት ቡድን ተው ሊባል ይገባል ብለዋል። የክልሉ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ ጠንካራ ህዝብ መሆኑን አንስተው መንግስት የህዝቡን ፍላጎት መሰረት አድርጎ ለማገዝና ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ከአሶሳ፣ አርሲ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን የክልሉን ህዝብ የሰላም መሻትና ለጥፋት የሚንቀሳቀሰውን የህወሃት ቡድን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡት ማብራሪያ ወሳኝ መልእክት የተላለፈበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የትግራይ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የፌደራሊዝም መምህር ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሰጠው ማብራሪያ የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ መሆኑን በማንሳት የህወሃት ቡድን ከዚህ በተቃራኒ ለግጭትና ጦርነት እያደረገ ያለውን ዝግጅት ያስገነዘበ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የክልሉ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል እንደሚገባ ተናግረዋል። የፌዴራል መንግስት ያሳየው ሆደ ሰፊነት የትግራይን ህዝብ የሰላም ፍላጎት የተረዳ እንዲሁም የጦርነትን አስከፊነት የተገነዘበ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በአርሲ ዩኒቨርሲቲ የባህልና ታሪክ ተመራማሪና መምህር ሙሐመድ ነሞ (ዶ/ር)፣ የትግራይ ህዝብ ለሰላም የተከፈተው በር እንዳይዘጋ ለጦርነት የሚቀሰቅስን የጥፋት ቡድን አጥብቆ መቃወምና መታገል አለበት ብለዋል። በቆየ አስተሳሰብ ተቸንክሮ የሚገኘው የህወሃት ቡድን የትግራይን ህዝብ ለብዙ ችግርና እንግልት እየዳረገው መሆኑን ገልጸው ከዚህ በኋላ ገለል ማለት እንዳለበት ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዐሕመድ (ዶ/ር) ማብራሪያ የህውሃት ቡድንን እኩይ ዓላማ ያጋለጠ እና የህዝቡን ሰላም፣ የመልማትና የተጠቃሚነት መብት መሰረት ያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ጳውሎስ ባልቻ፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግሥት ለሰላምና ልማት ያለውን ጠንካራ አቋም ያመላከተ መሆኑን ገልጸዋል። ከሰሞኑን ለትግራይ ህዝብ ያስተላለፉት መልእክት ለክልሉ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነት የመንግስትን ተግባራዊ ጥረት ያሳየ ነው ብለዋል። ከዚህ በመነሳት የትግራይ ህዝብና በተለይም ወጣቱ ጦርነትን በመቃወም ለሰላምና ልማት በመትጋት የመንግስትን ጥረት መደገፍና ማገዝ እንዳለበት አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልእክታቸው የትግራይ ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁ መምከራቸው ይታወቃል።
ፖለቲካ
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ዝግጁ ነን - የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 54
መቱ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ዘንድሮ በሚካሄደው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን በኦሮሚያ ክልል የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ። ካርድ ወስደን በመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል -የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም የሚካሔደው ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ እየሰራ ይገኛል። ከዝግጅቶቹ መካከል ከነገ የካቲት 28/2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሔደው የመራጮች ምዝገባ ተጠቃሽ ነው። ቦርዱ በአጠቃላይ ከሚኖሩት የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17ሺህ ያህሉ የዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቦር ዞን የሁሩሙ ወረዳ ነዋሪዋ ህዝባለም ደገፉ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ መብቴን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ እየተጠባበኩ ነው ብለዋል። የመቱ ወረዳ ነዋሪዋ ዝማርጉ ጀማል እና ናሐዊ ደፋር በበኩላቸው፤ በመራጭነት ተመዝግበው መብታቸውን ለመጠቀም እንዲችሉ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ምርጫ ለሀገረ መግሥት ግንባታ ወሳኝ ምእራፍ በመሆኑ የዜግነት ግዴታዬን በኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ ነኝ የሚለው ደግሞ የመቱ ከተማ ነዋሪው ወጣት በፈቃዱ እንዳለ ነው። ወጣት ፌዴሳ ታረቀኝ እና ግርማ ፍሪሳ በበኩላቸው፤ ጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እንደ ወጣት የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል። በሀገረ መንግስት ግንባታ ውስጥ ሴቶችና ወጣቶች የሚኖራቸው ሚና የላቀ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ በመውሰድ የሚወክለንን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። በተለይም በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚውና በማህበራዊ ዘርፎች ዘላቂ ተጠቃሚነታችን የሚያረጋግጥልን ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት የመራጮች ምዝገባ እስኪጀመር እየጠበቅን ነው ብለዋል።
የጥፋት ቡድኑን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን - የትግራይ ተወላጆች
Mar 6, 2026 99
ሐረር/አሶሳ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለጥፋት የቆመውን የህወሓት ቡድን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በሐረር እና በአሶሳ ከተሞች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ። የትግራይ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሰሞኑን በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ እንደሆነ ጠቁመው የሰላም እና ልማት ፍላጎቱ ትልቅ መሆኑን ገልጸዋል። በሁሉም ክልሎች እየመጣ ያለው ልማትና ሰላም የትግራይ ህዝብም ይገባዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአረጀ አስተሳሰብ ለዳግም ጦርነትና ውድመት የሚጥረው የሕወሓት ቡድን ተው ሊባል ይገባል ማለታቸው ይታወሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ በሐረር እና በአሶሳ ከተሞች ኢዜአ ያነጋገራቸው የትግራይ ተወላጆች፤ የህወሓት ቡድን ከጥፋትና የጦርነት እቅድ በስተቀር ለህዝብ ሰላምና ልማት መስራት የማይፈልግ ስብስብ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቡድኑን እኩይ ዓላማ እና የህዝቡን የሰላምና የልማት ፍላጎት በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ ተክክለኛ እና ወቅታዊ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ በመደገፍ ለጥፋት የቆመውን ቡድን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን ነው ያሉት። በሐረር ከተማ የሚኖሩት ወይዘሮ ጊዮርጊስ ሃጎስ፤ የጥፋት ቡድኑ መቼም ቢሆን ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ልማት ሰርቶ የማያውቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት ከማይሻው የሻዕቢያ መንግስት ጋር ግንባር በመፍጠር አካባቢውን የጦርነት ቀጣና ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸው ይህንን እኩይ ዓላማ በፅኑ እንታገለዋለን ብለዋል። የአሶሳ ከተማ ነዋሪው ጎይቶም በየነ፤ የህወሓት የጥፋት ቡድን እሳቤ ጊዜው ያለፈበትና ለማንም የማይጠቅም መሆኑንና የትግራይ ህዝብ አሁን ላይ እንደሌሎች ክልሎች በአዲስ እሳቤና በአዲስ ትውልድ መመራትን አጥብቆ ይሻል ብለዋል። በመሆኑም የህወሓትን ቡድን ጊዜው ያለፈበት አስተሳሰብ በጋራ በመታገል ለክልሉ ሰላም፣ ልማትና ተጠቃሚነት በተባበረ አቅም እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። በሐረር ከተማ የሚኖረው ሼኖክ ሊላይ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ያስተላለፉት መልእክት ለሀገር ሰላምና ልማት የሚጠቅም በመሆኑ ሁላችንም የምንደግፈው ነው ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደ ሌሎች ክልሎች ሁሉ ለትግራይ ክልል ህዝብ ሰላም፣ ልማትና እድገት ያስፈልገዋል ማለታቸው ተገቢ መሆኑን አንስቶ ለዚህም በተለይም የክልሉ ተወላጆች የበኩላችንን እንወጣለን ሲል ተናግሯል። ሌላኛው በአሶሳ ከተማ የሚኖረው ወጣት ክብሮም ገብረመድህን፤ በኢትዮጵያ ከመጣው ለውጥና ሁለንተናዊ የልማት እቅዶች ተጠቃሚ ለመሆን የትግራይ ህዝብ አጥብቆ ይሻል ሲል ገልጿል። ይህንን እውን ለማድረግ ደግሞ ለግጭትና ጦርነት እየሰራ የሚገኘውን የህወሓት የጥፋት ስብስብን በጋራ መታገል ሲቻል ብቻ መሆኑን ገልፆ ለዚህም በተለይ ወጣቶች አደራችንን ለመወጣት እንሰራለን ብሏል። በሐረር ከተማ ያገኘናቸው ወጣት ሳሙኤል መለስ እና ወጣት ፍሬህይወት ብርሃነ፤ የትግራይ ወጣቶች አሁን ላይ የህወሓትን የጦርነት ነጋሪት ሸሽተው እየተሰደዱ መሆኑን አንስተው ነገር ግን ስደት መፍትሄ የማያመጣ በመሆኑ ለትግራይ ህዝብ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና ለውጥ እንዲመጣ በትብብር እንሰራለን ብለዋል።
ካርድ ወስደን በመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል -የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 120
ሚዛን አማን፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለምርጫው ካርድ በመውሰድ ይበጀናል የሚሉትን የመምረጥ ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሂደት ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተሻለ ሀሳብ ያለው ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - ነዋሪዎች ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች፤ ለምርጫው ካርድ በመውሰድ ይበጀናል የሚሉትን አካል የመምረጥ ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ይረፉ መሸሻ ፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም የሚሰራ ፓርቲን ለመምረጥ ከወዲሁ ዝግጅት እያደረግን ነው ብለዋል። በምርጫው በመሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እንደሚወስዱም ገልጸዋል፡፡ ወይዘሮ ሶስና ሀብተማርያም የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ በበኩላቸው፤ በምርጫ መሳተፍ ሕገ መንግስቱ የሰጠን ዲሞክራሲያዊ መብት መሆኑን በመረዳት እየተዘጋጀን ነው ብለዋል። የሚወክለኝን ፓርቲ ለመምረጥ የምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሐ ግብር መሠረት ተመዝግቤ ካርድ ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ ነው ያሉት። የሀገረ መንግሥት ግንባታን የማጠናከር አንዱ አካል የሆነው የምርጫ ሥርዓት ላይ መሳተፍ ከአንድ ዜጋ የሚጠበቅ ኃላፊነት ነው ያለው ደግሞ ወጣት መልካሙ አሰፋ ነው። ከሕዝብ ጋር ሆኖ የተሻለች ኢትዮጵያን ይፈጥራል የሚለውን ፓርቲ ለመምረጥ በሀሳብ ላይ የተመሠረተ ዝግጅት ማድረጉን ተናግሯል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ አለማየሁ ሻርንስ ምርጫ ዜጎች የሀገራቸው የነገ ዕጣ ፈንታ ላይ የሚወስኑበት ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት የሚመሠረተው በምርጫና ምርጫ ብቻ በመሆኑ ለአካባቢ ልማትና ዕድገት የተሻለ አማራጭ ይዞ የሚመጣን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል። ኢዜአ ተዘዋውሮ እንደተመለከተው ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሚዛን ተፈሪ ምርጫ ክልል በተለያዩ ቀጠናዎች የምርጫ ጣቢያ የማደራጀት ሥራ ተከናውኗል።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተሻለ ሀሳብ ያለው ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 93
ጅግጅጋ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለሀገሪቱ ዕድገትና ለህዝቦች ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጀምር ማስታወቁ ይታወሳል ለመራጭነት የሚያበቃንን ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች፤ በመጪው ግንቦት 24 በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚችሉበትን ካርድ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለህዝብና ለሀገር ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም አስታውቀዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ጀማል ኢብራሂም፤ በአምስት ዓመት አንዴ የሚካሄደው ምርጫ ዜጎች ለሀገርና ህዝብ ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ የሚመርጡበትን ዕድል የሚያመቻች መሆኑን ተናግረዋል። በሶማሌ ክልል በአሁኑ ወቅት ያለው ሠላምና ፀጥታ ከዚህ ቀደም ከነበሩ ምርጫዎች በተሻለ መልኩ ለመሳተፍና ድምጽ ለመስጠት ሰፊ ዕድል መፍጠሩን ገልጸው፤ ይህንን ተጠቅመው በንቃት እንደሚሳተፉም አረጋግጠዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ መሀመድ ዑመር በበኩላቸው፤ ጠቅላላ ምርጫው የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማፋጠንና ለሀገር ዕድገት የሚረዳ ወሳኝ ሥርዓት መሆኑን ገልጸዋል። ለሀገር ይጠቅማል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል። በጠቅላላ ምርጫው ለመራጭነት የደረሱ ዜጎች በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸውም አክለዋል። ምርጫ የአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መገለጫ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ፈርሃን ሙሀመድ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። ካርድ በመውሰድ ለሀገር ዕድገት ይሰራል፤ የዜጎችን ህይወት ይለውጣል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙ ተናግረዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ለመራጭነት የሚያበቃንን ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል
Mar 6, 2026 78
ሀዋሳ/ቦንጋ/ሰመራ/አምቦ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ አካባቢ ነዋሪዎች ገለጹ። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ የጊዜ ሰሌዳዎችን ከማስቀመጥ ጀምሮ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እያከናወነ ነው። ከነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የመራጮች ምዝገባ የሚጀመር በመሆኑም ኢዜአ የመራጮችን ዝግጅትን አስመልክቶ በተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎችን አነጋግሯል። የቦንጋ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ነስረዲን ሀሰን፤ በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሔደው ምርጫ ተመዝግበው ካርድ ለመውሰድና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም እየተጠባበቁ መሆኑን ገልፀዋል። ''በግሌም ይሁን ለአካባቢያችን እና ለሀገር የሚበጅ ፓርቲ በመምረጥ ሂደት የእኔ ድምፅ ዋጋ እንዳለው ስለምረዳ ለመምረጥ የሚያበቃኝን ካርድ ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ'' ነው ያሉት። የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ እናኑ ከተማ፤ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚዲያ ስለፕሮግራማቸው የሚያስተላልፉትን ሀሳብ በመከታተል ይበጀኛል ያሉትን ለመምረጥ ከወዲሁ እየተዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል። በምርጫው ለመሳተፍ ዝግጁ ሆነው በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን የተናገሩት ወይዘሮ እናኑ ለእኔም ሆነ ለሀገር ይበጃል የምለውን ፓርቲ እመርጣለሁ ብለዋል፡፡ በዘንድሮው ምርጫ በድምጻቸው የሚበጃቸውን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ የመራጮች ምዝገባ ቀንን እየተጠባበቁ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሠመራ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ሐዋ አብዱ ናቸው። በተለይም ሴቶች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በመራጭነት በመሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸውም አስረድተዋል። በምዕራብ ሸዋ ዞን የቶኬ ኩታዬ ወረዳ ነዋሪ ወጣት ቢንያም አሸቱ፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ካርድ ለመውሰድ የምዝገባውን መጀመር እየተጠባበቀ መሆኑን ነው የተናገረው።
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል
Mar 6, 2026 126
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ የምርጫ ካርዳቸውን በወቅቱ በመያዝ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ወጣቶች እና ሴቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፣ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ዴሞክራሲያዊና በቴክኖሎጂ የታገዘ ሆኖ እንዲካሄድ በርካታ አስቻይ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል በዚህም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች አስፈላጊ የምርጫ ቅድመ ዝግጅት ስራዎችንም እየተከናወኑ ይገኛሉ። በተጨማሪም፣ በቦርዱ መርሀ ግብር መሠረት የመራጮች ምዝገባ ሂደት ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ይጀመራል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች እና ሴቶች ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት እየተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ወጣት ማርቆስ እሸቱ ከዚህ ቀደም በተካሄዱ ምርጫዎች ላይ በመሳተፍ እንደ ዜጋ ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የሚጠበቅበትን መወጣቱን ተናግሯል። ዘንድሮ የሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ካለፉት ጊዜያት በተሻለ የሚጠበቅበትን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ነው የተናገረው። ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ዘሀራ በርጋ፤ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግና የምሰጠው ድምጽ ዋጋ እንደሚኖረው በማወቅ ይበጀኛል የምለውን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብላለች። በተለይም ሁሉም ወጣት ይበጀኛል ወይም ተጠቃሚነቴን ያረጋግጥልኛል የሚለውን ፓርቲ መምረጥ እንዳለበት ገልጻለች፡፡ ወጣት አህመድ አሊ በበኩሉ፤ ወጣቱ ምርጫ ለአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ዕድገት ያለውን ጉልህ ፋይዳ በሚገባ ሊገነዘብ እንደሚገባ አንስቷል። የዴሞክራሲ ባህላችን ሊያድግ የሚችለው በወጣቶች ተሳትፎ ነው ሲልም ጨምሮ ተናግሯል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ የውብዳር ተመስገን፤ ምርጫ ተጠቃሚነትታችንን የምናረጋግጥበት መንገድ በመሆኑ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ ብላለች። መምረጥ ሕገ-መንግስታዊ መብት መሆኑን በመጥቀስ፣ ይህንን ዕድል በመጠቀም ለዴሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ የበኩሉን ሚና እንደሚወጣ የገለፀው ደግሞ ወጣት ዮሴፍ አበራ ነው። የመምረጥ መብቱን ለማረጋገጥም የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ሀላፊ ሙህዲን ናስር ፌዴሬሽኑ ቀደም ባሉት ምርጫዎች ወጣቱን በማንቃት ረገድ አዎንታዊ አስተዋፅኦ ማበርከቱን አስታውሰዋል። ዘንድሮ የሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን በተለይም ወጣቶችና ሴቶች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በተለያዩ አማራጮች ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
የአካባቢያችንን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የልማት ተሳትፏችንን እናጠናክራለን
Mar 5, 2026 145
ወልዲያና ባህር ዳር ፤ የካቲት 26/2018(ኢዜአ)፦ የአካባቢያችንን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ የልማት ተሳትፏችንን እናጠናክራለን ሲሉ የባህር ዳር እና ወልዲያ ከተሞች የመንግስት ሰራተኞች ገለጹ። የተጀመሩ የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ የድርሻችንን እንወጣለን- የሐይማኖት አባቶችና የመንግስት ሰራተኞች የወልዲያና የባህር ዳር ከተሞች አስተዳደሮች የመንግስት ሰራተኞች "ለሰላም ዘብ እንቆማለን፤ የልማት አርበኛም እንሆናለን" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ውይይት አካሄደዋል። በወልዲያ ከተማ በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ የተሳተፉት አቶ አሳዬ በላይነህ እንደገለጹት፤ ጸረ ሰላም ሀይሎችን በመመከት ድርሻቸውን ለማጠናከር ተዘጋጅተዋል። የአካባቢን ሰላም በዘላቂነት በማረጋገጥ የአገርን እድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግ ሁሉም ዜጋ በየተሰማራበት የሥራ መስክ መትጋት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ፈንታው አዲሱ በበኩላቸው አገራቸውን ክደው ከጠላት ጋር የሚያብሩ ኃይሎች ከባንዳነት ያለፈ ታሪካዊ ጠላቶች ናቸው ብለዋል። በአካባቢያቸው ሰላም እንዲሰፍን እና ልማት እንዲፋጠን በአንድነት መቆም እንደሚገባም አመልክተዋል። በብልጽግና ፓርቲ የወልዲያ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ገብሬ፤ የውስጥ ባንዳዎችንና የውጭ ጠላቶችን ሴራ በመመከት አገርን ከነክብሯ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል። ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የመንግስት ሰራተኛው የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል። በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው ውይይት ላይ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ግዛቸው፤ ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት መሆኑን ገልፀዋል። የመንግስት ሰራተኛው ሰላምን አፅንቶ ማስቀጠልና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እንዲሁም የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የሚሰሩ ስራዎች ውስጥ እየተወጣ ያለውን ሚና ማጠናከር አለበት ብለዋል። በተጨማሪም የመንግስት ሰራተኛው በሰዓቱ በመገኘትና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህዝብ ቅሬታዎችን ማስወገድ እንዳለበት አመልክተዋል። በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አሁን ያለውን ሰላም አፅንቶ ማስቀጠል እንደሚገባም አሳስበዋል።
የትግራይ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል
Mar 5, 2026 106
አሶሳ/አዳማ/ሶዶ፤ የካቲት 26/2018(ኢዜአ)፦ የትግራይ ክልል ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቀናት በፊት ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ መሆኑን አንስተው የሰላም እና ልማት ፍላጎቱ ትልቅ መሆኑንም ገልጸዋል። የሰሜኑ ጦርነት የተከሰተው ህወሓት ለውጥን ባለመቀበሉ እና ያረጀ እሳቤን የማስቀጠል አባዜ ምክንያት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሁሉም ክልሎች እየመጣ ያለው ልማትና ሰላም የትግራይ ህዝብም ይገባዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአረጀ አስተሳሰብ ለዳግም ጦርነትና ውድመት የሚጥረው የህወሃት ቡድን ተው ሊባል ይገባል ብለዋል። የክልሉ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ ጠንካራ ህዝብ መሆኑን አንስተው መንግስት የህዝቡን ፍላጎት መሰረት አድርጎ ለማገዝና ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ከአሶሳ፣ አርሲ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን የክልሉን ህዝብ የሰላም መሻትና ለጥፋት የሚንቀሳቀሰውን የህወሃት ቡድን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡት ማብራሪያ ወሳኝ መልእክት የተላለፈበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የትግራይ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የፌደራሊዝም መምህር ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሰጠው ማብራሪያ የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ መሆኑን በማንሳት የህወሃት ቡድን ከዚህ በተቃራኒ ለግጭትና ጦርነት እያደረገ ያለውን ዝግጅት ያስገነዘበ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የክልሉ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል እንደሚገባ ተናግረዋል። የፌዴራል መንግስት ያሳየው ሆደ ሰፊነት የትግራይን ህዝብ የሰላም ፍላጎት የተረዳ እንዲሁም የጦርነትን አስከፊነት የተገነዘበ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በአርሲ ዩኒቨርሲቲ የባህልና ታሪክ ተመራማሪና መምህር ሙሐመድ ነሞ (ዶ/ር)፣ የትግራይ ህዝብ ለሰላም የተከፈተው በር እንዳይዘጋ ለጦርነት የሚቀሰቅስን የጥፋት ቡድን አጥብቆ መቃወምና መታገል አለበት ብለዋል። በቆየ አስተሳሰብ ተቸንክሮ የሚገኘው የህወሃት ቡድን የትግራይን ህዝብ ለብዙ ችግርና እንግልት እየዳረገው መሆኑን ገልጸው ከዚህ በኋላ ገለል ማለት እንዳለበት ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዐሕመድ (ዶ/ር) ማብራሪያ የህውሃት ቡድንን እኩይ ዓላማ ያጋለጠ እና የህዝቡን ሰላም፣ የመልማትና የተጠቃሚነት መብት መሰረት ያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ጳውሎስ ባልቻ፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ መንግሥት ለሰላምና ልማት ያለውን ጠንካራ አቋም ያመላከተ መሆኑን ገልጸዋል። ከሰሞኑን ለትግራይ ህዝብ ያስተላለፉት መልእክት ለክልሉ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነት የመንግስትን ተግባራዊ ጥረት ያሳየ ነው ብለዋል። ከዚህ በመነሳት የትግራይ ህዝብና በተለይም ወጣቱ ጦርነትን በመቃወም ለሰላምና ልማት በመትጋት የመንግስትን ጥረት መደገፍና ማገዝ እንዳለበት አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልእክታቸው የትግራይ ወጣቶች የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑና በአሮጌ አስተሳሰብ ለጦርነት ከሚገፋፏቸው አካላት ራሳቸውን እንዲጠብቁ መምከራቸው ይታወቃል።
ማህበራዊ
በክልሉ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የኃይማኖት አባቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል-ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Mar 6, 2026 34
ባሀርዳር፤የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በስነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ በመገንባት ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የኃይማኖት አባቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለፁ። "የመደመር መንግስት እና የኃይማኖት ተቋማት ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ ከወንጌላዊያን፣ ካቶሊክና ከ7ኛ ቀን አድቬንቲስት የሃይማኖት መሪዎች ጋር ክልላዊ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው። ርዕሰ መስተዳደሩ አቶ አረጋ ከበደ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፤ የኃይማኖት አባቶች የተረጋጋ ሀገረ መንግስት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ሚናቸው ከፍተኛ ነው። በተለይም ለተከታዮቻቸው ሰላምን በመስበክ፣ ትውልዱን በስነ-ምግባር በማነፅና በመገንባት ያላቸውን ሚና በተሻለ መንገድ መወጣት እንደሚገባቸው ነው የተናገሩት። ኢትዮጵያ የብዝሃ ኃይማኖትና ቋንቋዎች ሀገር በመሆኗ ይህንን ጸጋ ለላቀ የሀገር ግንባታ ለማዋል በጋራ መስራት አሰፈላጊ በመሆኑ የውይይት መድረኩ መዘጋጀቱን ገልፀዋል። የኃይማኖት አባቶች በክልሉ የሚስተዋሉ የሰላም ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራትም የተሻለ አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው ያመለከቱት። የኃይማኖት አባቶች እስካሁን ለመጣው ሰላምና ልማት የጎላ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን ጠቁመው በቀጣይም ይህንኑ አጠናክረው መቀጠል እንደሚጠበቅባቸው ነው ያሳሰቡት። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኃይማኖት አባቶች ለሀገረ መንግስት ግንባታ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ለሀገር ሰላምና ለትውልድ ግንባታ አበርክቷቸው ከፍተኛ በመሆኑም ሰላምን ለማጽናት በሚደረገው ጥረት ድርሻቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል። በተለይም ገዥ ትርክት ላይ የተመሰረተ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለመገንባት መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት ስኬታማ እንዲሆንም ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። በሀገራዊና ህዝባዊ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የዕምነት አባቶችና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
የሆስፒታሎች ጥምረት የአገልግሎት ጥራትንና ትስስርን በማጠናከር የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ አስችሏል
Mar 6, 2026 53
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት መርሃግብር የሆስፒታሎችን ትስስር በማጠናከር የተገልጋዮች እርካታን ማሳደግ እያስቻለ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። በታዳሽ ኃይል የታገዘ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋፋት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል አራተኛው ዙር የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት የሽልማት ስነ-ስርዓት እንዲሁም የአምስተኛ ዙር የሆስፒታሎች ጥምረት የትኩረት አቅጣጫ ማስተዋወቂያ እና ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል። በዚህ ወቅት የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እንዳሉት፤ መንግስት የጤና ዘርፉን ጥራት ያለው፣ ፍትሃዊና ተደራሽ ለማድረግ ሲሰራ ቆይቷል። በተለይ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኃላ የድንገተኛ ህክምናና ፅኑ ህሙማን ህክምና ላይ መሻሻል መምጣቱን ገልፀው፤ የግል ጤና ተቋማት ቁጥር በሶስት እጥፍ ማደጉን ተናግረዋል። ለ70 ዓመታት ያህል በአንድ አምራች ሲቀርብ የነበረው የኦክሲጅን ምርት በኮቪድ ወቅት 3 እንደነበር ጠቅሰው አሁን ላይ 64 የኦክሲጅን ፕላንት መኖሩን ገልፀዋል። የሀገር ውስጥ የመድኃኒት አቅራቢዎች ቁጥር ማደጉንና የህክምና ግብዓትና መድኃኒት ስርጭትም መሻሻል እያሳየ መሆኑን አስረድተዋል። ከ5ሺህ በላይ የጤና ተቋማት ውል ወደተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት መግባታቸውን ጠቅሰው፤ የእናቶችና ህፃናት ሞትም እየቀነሰ መምጣቱን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት መርሃግብር የሆስፒታሎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻልና የተገልጋዮች እርካታን እያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል። መርሃግብሩ በጤና ተቋማት መካከል ያለውን የእርስ በርስ ትብብር ማጠናከር ያስቻለ መሆኑን ጠቅሰው፤ የተገልጋይ እርካታ አሁን ላይ 85 በመቶ መድረሱንም ተናግረዋል። አራተኛው ዙር መርሃግብር በመረጃ ላይ የተደገፈ የህክምና አገልግሎት ላይ ያተኮረ እንደነበር አውስተው፤ ከዚህ ቀደም የተተገበሩ አራቱም ዙሮች ክፍተቶችን ማሟላት ላይ ያተኮሩ እንደነበርም አንስተዋል። አምስተኛው ዙር የተሟላ ህክምና አገልግሎት ላይ በማተኮር የተጀመሩ ማሻሻያዎችን ማጠናከር የሚያስችልና የሰው ኃይል ልማት ላይ አተኩሮ የሚተገበር እንደሚሆንም ጠቁመዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በበኩላቸው፤ ጤናማና አምራች ዜጋ ለሀገር ብልፅግና ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። ለጤናው ዘርፍ ከተሰጡት ተልዕኮ አንዱ ጥራት ያለው አገልግሎት በፍትሃዊነት ማዳረስ መሆኑን አንስተው ለዚህም ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት መርሃግብር በሆስፒታሎች መካከል ጤናማ ውድድር እንዲኖር በማድረግ የአገልግሎት መሻሻል እንዲመጣ እያስቻለ ነው ብለዋል።
የመደጋገፍ እና የመረዳዳት እሴትን ለማጠናከር ሁሉም ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል
Mar 5, 2026 94
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018(ኢዜአ)፦ የመደጋገፍ እና የመረዳዳት እሴትን ለማጠናከር በሚከናወኑ ተግባራት ሁሉም ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሊወጡ እንደሚገባ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጋር በመተባበር ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን ለመርዳት ያለመ "የረመዳን ሶሊዳሪቲ" የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ፈርመውታል። ሚኒስትሯ ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በመርሃ-ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ረመዳን የጾም፣ የጸሎትና የማካፈል ወር መሆኑን ጠቅሰዋል። መንግስት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰፋፊ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸው፤ ውስብስብ ጉዳዮችን በጋራ ለመፍታት የሁሉንም አካላት ተሳትፎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ ስምምነቱ ለረመዳን ወር ብቻ ተገድቦ የሚቀር ሳይሆን፤ ወደፊትም ሌሎች አካላትን በማካተት ተጠናክሮ የሚቀጥል ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በበኩላቸው፤ መተጋገዝ እና መረዳዳት የሰው ልጅ ግዴታ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። መረዳዳት በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸው፤ ሚኒስቴሩ ያቀረበው ሃሳብ መልካም ዓላማ ያለው በመሆኑ ሁሉም ዜጋ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል። ይህ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር በዋናነት ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በዘላቂነት መደገፍ፣ የአብሮነት እና የመረዳዳት እሴትን ማጠናከር እንዲሁም ለጋራ ዓላማ በጋራ መቆም እንደሚቻል በተግባር ማሳየትን ያለመ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ሚና አጠናክረው መቀጠል አለባቸው
Mar 5, 2026 84
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018(ኢዜአ)፦የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ሚና አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያስላሴ ገለጹ፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የማይተካ ሚና አላቸው አምስተኛው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት "ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላምና አካታች ልማት " በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተከፍቷል። በመክፈቻ መርኃግብሩ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን ቢራቱ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የፍትህ ሚኒስትር ሃና አርዓያስላሴ በዚሁ ወቅት፤ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የሕግና የአሠራር ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ጨምረዋል፡፡ ይህም የሆነው መንግሥት የዜጎችን የመደራጀት መብት ለማረጋገጥ የህግና የአሰራር የአዋጅ ማሻሻያ ማድረጉን ተከትሎ ነው ብለዋል። ሲቪል ማኅበራት አካታች ሀገራዊ ምክክር፣ የሽግግር ፍትህ ሂደት እና ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ጉዳዮች ላይ የማይተካ ሚና እንዳላቸው አፅንዖት ሰጥተዋል። እነዚህ ኹነቶች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለዘላቂ ሰላም ያላቸው ፋይዳ የላቀ በመሆኑ ድርጅቶቹ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። ሲቪል ማኅበራት አሠራራቸውን በግልጽነትና በተጠያቂነት ላይ መመሥረት እንዳለባቸው ሚኒስትሯ አሳስበዋል። የጋራ ቤታችን የሆነችውን ሀገር ለማፅናት የተናበበ ጥረታችን ሊጠናከር ይገባል ያሉት ሚኒስትሯ መንግሥት ለዘርፉ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ዛሬ የሚገነባው ሰላምና ልማት ለቀጣዩ ትውልድ መሠረት በመሆኑ መንግሥት ከሲቪል ማኅበራት ጋር ያለውን አጋርነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ኤግዚቢሽኑ ከዛሬ የካቲት 26 እስከ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።
ኢኮኖሚ
የከተማውን ሰላምና ልማት በማስጠበቅ ረገድ የንግዱ ማህበረሰብ እያበረከተ ያለውን ሚና እንዲያጠናክር ተጠየቀ
Mar 6, 2026 10
ባህር ዳር፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፡- የባህር ዳር ከተማን ሰላምና ልማት በማስጠበቅ ረገድ የንግዱ ማህበረሰብ እያበረከተ ያለውን ሚና የበለጠ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው የከተማ አስተዳደሩ አስገንዝቧል። የከተማ አስተዳደሩ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በከተማዋ ከሚገኙ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አካሄዷል። በውይይት መድረኩ ላይም የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ እንዳሉት የከተማውን ሰላምና ልማት በማስጠበቅ ረገድ የንግዱ ማህበረሰብ እያበረከተ ያለውን ሚና አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። በከተማዋ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች ሰፋፊ የህዝብን ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ የሚችሉ የልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑና እየተፋጠኑ መሆኑን ገልጸዋል። የንግድ ማህበረሰብም በከተማዋ እየተከናወኑ ባሉ የኮሪደርም ሆነ ሌሎች የልማት ስራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑን አውስተዋል። በክልሉ አሁን ላይ የሰፈነውን ሰላም በማፅናት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የንግዱ ማህበረሰብ የተጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል። በመሆኑም ለከተማዋ ሰላምና ልማት መረጋገጥ እያበረከተ የሚገኘውን አስተዋፅኦ አጠናክሮ ሊያስቀጥል እንደሚገባም ምክትል ከንቲባው አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ጌጡ አንዳርጌ እንደገለጹት፤ የከተማውን ሰላምና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ነጋዴው ማህበረሰብ በተደራጀ አግባብ እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል። ሌላኛዋ ተሳታፊ ወይዘሮ ዋጋ አዘዘ በበኩላቸው በከተማዋ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ እየተደረገ ባለው ጥረት እየተወጣን የምንገኘውን ሚና እናጠናክራለን ብለዋል። በመድረኩ በከተማው በተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ ነጋዴዎችና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።
በዞኑ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል ይደረጋል
Mar 6, 2026 36
አምቦ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሸዋ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች የበለጠ ውጤታማ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉ በዞኑ ምልከታ ያደረጉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የጨፌ ኦሮሚያ አባላት ተናገሩ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የጨፌ ኦሮሚያ አባላት በዞኑ በቶኬ ኩታዬ፣ በኢሉ ገላን እና በባኮ ወረዳዎች በኩታ ገጠም የለማ የሙዝ፣ የፓፓያ፣ የበጋ ስንዴና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። አባላቱ ከጉብኝቱ በኋላ በዞኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት እንዲጠናከሩ የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የዳኖ ምርጫ ክልል ተወካይ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር)፤ በዞኑ እየተከናወኑ ከሚገኙ የልማት ስራዎች በተለይም በግብርናና በሌሎች ልማቶች ላይ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሥራዎቹ በቴክኖሎጂ እንዲደገፉና አስፈላጊ ግብዓቶች እንዲሟሉላቸው ድጋፍ እና ክትትል በማድረግ የሀገሪቱን እድገት በማፋጠን ረገድ የራሳቸውን ድርሻ እንደሚወጡም ተናግረዋል። ሌላዋ የጨፌ ኦሮሚያ አባልና የባኮ ምርጫ ክልል ተወካይ ወይዘሮ ኤቢሴ ፍርዲሳ በበኩላቸው፤ በዞኑ ከዚህ ቀደም ተሰርተው የማያውቁ ትላልቅ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውንና ለሕብረተሰቡ የሥራ ዕድል መፈጠሩን መታዘባቸውን ገልጸው፣ ይህም የሀገሪቱን እድገት እንደሚያፋጥን ተናግረዋል። በተጨማሪም የሕዝብና የመንግሥት ሀብት ከሌብነትና ከብክነት በጸዳ መልኩ ለልማት እንዲውል አስፈላጊውን ክትትል እንደሚያደርጉና ሁሉም በዚህ ላይ እንዲሳተፍ መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የጨፌ ኦሮሚያ አባላት ባደረጉት ጉብኝት ለሰጡት ገንቢ አስተያየት ያመሰገኑት የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አበበ ጨመዳ ናቸው። የቀረቡትን ገንቢ ሐሳቦች በመጠቀም በዞኑ ከዚህ በላይ ያሉ የልማት ሥራዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በጥራትና በትኩረት ለመሥራት መታቀዱን ገልጸዋል። በዞኑ የተሰሩ የልማት ሥራዎች አበረታች ቢሆኑም፣ ከዚህ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከሕብረተሰቡ እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ይጠናከራሉ ብለዋል። በልማት ስራዎች የመስክ ምልከታው ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የጨፌ ኦሮሚያ አባላትን ጨምሮ የዞኑ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
አርሶ አደሩ በበልግ ወቅት የሚጠበቀውን የዝናብ ስርጭት ተጠቅሞ የሰብል ምርታማነቱን ማሳደግ አለበት
Mar 6, 2026 41
ደሴ ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦አርሶ አደሩ በበልግ ወቅት የሚጠበቀውን መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ተጠቅሞ የሰብል ምርታማነቱን ማሳደግ እንዳለበት በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምስራቅ አማራ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አስታወቀ። በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ ነው የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ በበኩሉ ከ104 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበልግ ዝናብ ለማልማት መታቀዱን አስታወቋል። በማዕከሉ የትንበያና ቅደመ ማስጠንቀቂያ ዴስክ ኃላፊ ወይዘሮ ሉባባ መሀመድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በልግ ለምስራቅ አማራ ቀጠና ከመኸር ቀጥሎ 2ኛው የምርት ወቅት ነው። ከተያዘው ወር መጨረሻ ጀምሮ ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ወሎ እና ሰሜን ሸዋ ዞኖችን ጨምሮ ምስራቅ አማራ ቀጠና መደበኛና ከመደበኛ በላይ የበልግ ዝናብ ይጠበቃል ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም በደቡብ ወሎ እና በሰሜን ወሎ ዞን ዝናብ መጣል መጀመሩን ጠቁመው፣ አርሶ አደሩ በበልግ የሚጥለውን ዝናብ በመጠቀም የዘር ሥራውን አጠናከሮ ማስቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። ለዚህም የበልግ ዝናብን በማሳው ዳርና ውስጥ ላይ በማቆር በደረቅ ወቅት ለመጠቀም የሚያስችል ዝግጅት እንዲያደርግም መክረዋል። እንደሃላፊዋ ገለጻ ፤የበልግ ዝናብ ለሰብል ልማት፣ የአፈር እርጥበትን ለማሻሻል፣ ለእንስሳት ግጦሽ፣ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። ቅጽበታዊ ጎርፍ፣ የሰብል በሽታና ተባይ ተከስቶ ጉዳት እንዳይደርስ አርሶ አደሩ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበትም አሳሰበዋል። በደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ በበኩላቸው፤በዞኑ በበልግ ወቅት ከ104 ሺህ 600 ሄክታር በላይ መሬት በተለያየ ሰብል እንደሚለማ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የበልግ ዝናብ በአካባቢው መዝነብ መጀመሩን ገልጸው፣ አርሶ አደሩም የዘር ሥራውን አጠናክሮ በማስቀጠል ምርታማነቱን እንዲያሳድግ እየተሰራ ነው ብለዋል። በበልግ እርሻ ምርታማነትን ለማሳደግም ለአርሶ አደሩ ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያና ሌሎች ግብአቶችን የማቅረብ ሥራ መሰራቱን አመልክተዋል፡፡ በበልግ ልማት እየተሳተፉ ካሉ የደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር ኢብራሂም በሽር፤ አንድ ሄክታር ማሳቸውን በበልግ ለማልማት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በእስካሁኑ የልማት ሥራም ለበልግ ያዘጋጁትን የተፈጥሮ ማዳበሪያ አለስልሰው ባዘጋጁት ማሳ መበተናቸውን ገልጸው፣ በመንግስት ሰው ሰራሽ ማዳበሪያም እንደቀረበላቸው ተናግረዋል። በዚሁ ዞን የለጋምቦ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ይማም አሊ በበኩላቸው፤ አንድ ሄክታር ተኩል ማሳቸው ላይ በበልግ ስንዴ፣ ገብስና ምስር ለማልማት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ባንግላዴሽ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የንግድና የኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ትሻለች - አምባሳደር ሲትዋት ናየም
Mar 6, 2026 82
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ባንግላዴሽ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆኗን በኢትዮጵያ የባንግላዴሽ አምባሳደር ሲትዋት ናየም ገለጹ። አምባሳደር ሲትዋት ናየም የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በጣም ጥሩ በሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። በተለይም ባንግላዴሽ እ.አ.አ በ2016 በኢትዮጵያ ኤምባሲ ከከፈተችበት ጊዜ አንስቶ ግንኙነቱ እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። ሁለቱ ሀገራት የኢኮኖሚ ትብብራቸውን ለማሳደግ የጋራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንዳላቸውም አንስተዋል። በቅርቡ የተካሄደው የባንግሌዴሽ እና የኢትዮጵያ የንግድ ትርኢት ሀገራቱ በዘርፉ ያላቸውን ትብብር ማጎልበት እንደሚቻል የታየበት ነው እንደነበርም ገልጸዋል። በትርኢቱ የባንግላዴሽ ባለሀብቶች ኢትዮጵያ በፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ላይ እንደሆነችና ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪ እና በፍጆታ እቃዎች ላይ ፍላጎቷ እያደገ መምጣቱን ለመረዳት መቻላችውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በጣም በፍጥነት እያደገችና የልማት ስራው አስደማሚ መሆኑን የገለጹት አምባሳደሩ ይህም ለባንግላዴሽ የንግድ ማህበረሰብ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር አመልክተዋል። ሀገራቱ የንግድ ትብብራቸውን ማጠናከር ከሚችሉባቸው መስኮች አንዱ ቡና መሆኑንም አንስተዋል። ኢትዮጵያ በቡና ወጪ ንግድ የምትታወቅ ሀገር መሆኗን ጠቁመው ባንግላዴሽ ቡናን ጠብቆ ማቆየት የሚያስችል ከተፈጥሮ ፋይበር(ቃጫ) የተሰራ ቦርሳ እንደምታመርትም ገልጸዋል። ይህ በሀገራቱ ያሉ የንግድ ማህበረሰቦች ተቀራርበው እንዲሰሩና የዘርፉን ትብብር ለማጎልበት እንደሚያስችል ነው ያብራሩት። ፋርማሲዩቲካልን ጨምሮ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ሌላኛው የትብብር አቅም እንደሆነም ጨምረው ተናግረዋል። የባንግላዴሽ ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ሰፊ ገበያ መግቢያ በር መሆኗን በመገንዘብ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱም ጥሪ አቅርበዋል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለባንግላዴሽ ኢትዮጵያን ጨምሮ አጠቃላይ በአህጉሪቱ ያላትን የገበያ ተደራሽነት መጨመር የሚያስችሉ እድሎች እንዳሉትም አምባሳደሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ባንግላዴሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1976 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢንስቲትዩቱ የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ ምርምሮችን እያከናወነ ነው
Mar 6, 2026 104
አዳማ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ የጥናትና ምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ አስራት እንደገለጹት፤ ተቋሙ በኦሮሞ ባህል፣ እሴት፣ ስነ-ጥበብ፣ ታሪክ፣ ቋንቋና እድገት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። ወጣቶች መልካም ስብዕናን ተላብሰው ለሀገር ልማት እና እድገት እንዲተጉ የባለድርሻ አካላት ሚና ሊጠናከር ይገባል ይህንንም ውጤታማ ለማድረግ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ከሚገኙ ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ከቱሪዝም ኮሚሽን፣ ከባህል ጥናት ማዕከል እንዲሁም ከወጣቶችና ስፖርት ቢሮዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ እስካሁን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ከ70 በላይ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ከእነዚህም መካከል በታሪክ፣ በቋንቋና በባህል ላይ ያተኮሩ ከ30 በላይ መጻሕፍት ታትመው ለማህበረሰቡ ተደራሽ ሆነዋል ብለዋል። እነዚህ ስራዎች በተለይም የወጣቶችን የማንበብ ባህል ለማጠናከርና ሁለንተናዊ ስብዕናቸው እንዲገነባ ለማስቻል ትልቅ ድርሻ እንዳላቸውም አመልክተዋል። የጥናት ውጤቶቹንና የመጻሕፍት ዝግጅቱን አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች፣ ስራው በትውልዱ ላይ የሚታየውን የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላት እንደሚረዳ ገልጸዋል። ወጣት ስራጅ አህመድ እንደገለጸው፣ ንባብ ወጣቶች ስለ ማህበረሰቡ ስብዕናና ባህል እንዲያውቁ ያደርጋል። የገዳ ስርዓት መሰረታችንና ማንነታችን ነው ያለው ወጣት ስራጅ፣ ስለ ስርዓቱና ስለ ኦሮሞ እሴቶች በቂ እውቀት ለማግኘት የንባብ ባህላችንን ማጎልበት ይገባናል ብሏል። ተተኪው ትውልድ ስራን ከመናቅ ወጥቶ በልማት ስራዎች ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለበትም ነው የገለጸው።
የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ “ንዋይ” የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያን ይፋ አደረገ
Mar 5, 2026 123
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (ESX) የካፒታል ገበያን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል “ንዋይ” የተሰኘ የሞባይል ግብይት መተግበሪያ ዛሬ ይፋ አድርጓል። መተግበሪያው በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ማንኛውም ግለሰብ በሞባይል ስልኩ በመጠቀም በአክሲዮን እና በዕዳ ሰነዶች ግብይት ላይ በቀጥታ እንዲሳተፍ እድል የሚሰጥ ነው። የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን እስማኤል (ዶ/ር) በመተግበሪያው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ እንደተናገሩት፤ "ንዋይ" ገበያውን በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እጅ ላይ ተደራሽ ያደርገዋል። መተግበሪያው ባለሀብቶች በማንኛውም ጊዜና ቦታ ሆነው በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ውስጥ በቀጥታ እንዲሳተፉ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው የሰነድ ግዢና ሽያጭ ትዕዛዞችን በስልክ ማስተላለፍና መፈጸም እንሚያስችልም ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተህልቁ በበኩላቸው በርካታ ሀገራት ወደዚህ ዓይነት የቴክኖሎጂ ሥርዓት ለመድረስ ረጅም ጊዜ እንደወሰደባቸው አስታውሰዋል። ኢትዮጵያ ግን ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ በመማር በአጭር ጊዜ ውስጥ ዘመናዊ የገበያ ሥርዓት መገንባቷን ገልጸዋል። ይህ ሥርዓት ልዩ የሚያደርገው አካታችነቱ ነው ያሉት ዳይሬክተሯ በሁሉም የሀገሪቱ ጫፍ ያሉ ዜጎች የኢንቨስትመንት አካውንት በመክፈት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ መንግስት ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው ግልጽና ተገማች የሆኑ ህጎች መውጣታቸው ለዚህ ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥራ አስፈጸሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር)፣ ገበያው ሁሉም ዜጋ በአቅሙ ልክ የሚሳተፍበት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። እንደ ቴሌ ብር እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) መተግበሪያዎች ያስመዘገቡት ስኬት ለ"ንዋይ" ውጤታማነት እንደ ማሳያ እንደሚጠቀስም ገልጸዋል። መተግበሪያውን በአሁኑ ወቅት በአንድሮይድ (Android) እና በአይኦኤስ (iOS) ስልኮች ላይ ለመጫን ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የካፒታል ገበያ ባለቤት ማድረግ ግብን ለማሳካት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያን ዲጂታል መሠረተ-ልማት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ስምምነት ተፈረመ
Mar 5, 2026 115
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮ ቴሌኮም የኔትወርክ ማስፋፊያን በማከናወን እና በማዘመን የኢትዮጵያን ዲጂታል መሠረተ-ልማት ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ከኤሪክሰን ኩባንያ ጋር ተፈራረመ። ስምምነቱ በኤሪክሰን የኔትወርክ አሥተዳደር ቀጣና ውስጥ በሚገኙ 1 ሺህ 500 የሞባይል ጣቢያዎች ላይ የማስፋፊያ፣ የማሻሻያ፣ የ4ጂ ንጣፍ እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የመገንባት ሥራዎችን ያካትታል ተብሏል። ይህ ሁለንተናዊ የማዘመን ኢኒሼቲቭ የኔትወርክ ሽፋንን፣ ጥራትንና ዐቅምን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሻሽል መሆኑን የኢትዮ ቴሌኮም መረጃ አመላክቷል። በዚህም ነባር መሠረተ ልማቶችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመተካት፤ የ4ጂ ሽፋን እና ዐቅምን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድግ መሆኑ ተጠቁሟል። የ5ጂ ተደራሽነትንም በማስፋት ለዘመናዊ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያስፈልገውን ከፍተኛ የፍጥነት ኮኔክቲቪቲ ዕውን ለማድረግ ያስችላል ነው የተባለው። በተለይም ፕሮጀክቱ 75 ለሚሆኑ የገጠር አካባቢዎች ተስማሚ የሆኑ የሞባይል ቴክኖሎጂ ሶሉሽኖችን ለማቅረብ እንደሚያስችልም ተመላክቷል። በተጨማሪም 502 ነባር የ3ጂ ጣቢያዎችን ለማዘመን እና ወደ ላቀ የ4ጂ ቴክኖሎጂዎች ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል። ፕሮጀክቱ በኤሪክሰን (Ericsson) የኦፕሬሽን ቀጣና ውስጥ 2 ነጥብ 8 ሚሊየን አዲስ የ4ጂ ኔትዎርክ የመሸከም ዐቅም ለመጨመር የሚያስችል ሲሆን፤ ይህም አጠቃላይ የኔትዎርክ ዐቅሙን ወደ 4 ነጥብ 1 ሚሊየን ለማድረስ ያስችላል ተብሏል። በተጨማሪም የኤልቲኢ (LTE) አገልግሎትን ወደ 157 ተጨማሪ ከተሞች በማስፋፋት፣ አጠቃላይ የኤልቲኢ አገልግሎት ተጠቃሚ ከተሞችን ቁጥር ወደ 276 ያደርሳል ብሏል ኢትዮ ቴሌኮም። ይህም ሽፋንን በ45 በመቶ በማሳደግ፤ በሪጂኑ ያለውን አጠቃላይ የሕዝብ ሽፋን 85 በመቶ ለማድረስ እንደሚያስችል ጠቁሟል። ስምምነቱ የኢትዮጵያውያንን የአኗኗር ዘይቤ፣ አሠራር እና ግብይት የሚያከናውኑበትን መንገድ ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገሩ የሚገኙ፤ እንደ ቴሌብር፣ ዘመን ገበያ እና ዘኔክሰስ ለመሳሰሉ ፕላትፎርሞች ድጋፍ ይሰጣል።
ማዕከሉ በተቋቋመ ስድስት ወራት ውስጥ ከ23 ሺህ በላይ ሰዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት አግኝተዋል
Mar 5, 2026 127
ድሬደዋ፣ የካቲት 26/2018(ኢዜአ) :-የድሬዳዋ መሶብ የአንድ ማዕከል በተቋቋመ ስድስት ወራት ውስጥ ከ23 ሺህ በላይ ሰዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸው ተገለጸ። የማዕከሉ አስተባባሪ አቶ አወቀ ለገሰ ለኢዜአ እንደገለጹት በመስከረም 2018 ስራ የጀመረው ማእከሉ በ10 ተቋማት 28 አገልግሎቶች እየተሰጡ ነው። ማእከሉ ስራ ከጀመረ ወዲህ ከ23ሺህ በላይ ሰዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ማእከሉ ከወረቀት ንክኪ የፀዳ ዘመናዊ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህዝብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል። በተሰራው የእርካታ ዳሰሳ ጥናት ህብረተሰቡ በመንግስት አገልግሎት ከፍተኛ እርካታ ማግኘት እንደቻለ መረጋገጡን አመልክተዋል። በማዕከሉ የተሰባሰቡ ተቋማት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ተገልጋዮች ናቸው። ከተገልጋዮች መካከል አቶ አብዲ ቡሽራ እንዳሉት በማዕከሉ የሚሰጡት ዲጂታል አገልግሎቶች አስደሳች መሆናቸውን ገልጸዋል። በማዕከሉ የይዞታ ካርታ ለማውጣት መጥተው ፈጣን አገልግሎት በማግኘታቸው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ አጠናቀው ወደ ስራቸው መመለስ እንደቻሉ ተናግረዋል። ቀደም ሲል ተቋማት በተለያዩ አካባቢዎች ተበታትነው ስለሚገኙ አንድ አገልግሎት ለማግኘት እስከ ሳምንት ጊዜ እንደሚፈጅና ብዙ ድካም ይጠይቅ እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ በመጣው ለውጥ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ወይዘሮ ሰላማዊት ሐጎስ በበኩላቸው ግብር ለመክፈል ወደ ማእከሉ መምጣታቸውን ጠቁመው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ መጨረሳቸውን ተናግረዋል ። ወደ ማእከሉ ጉዳይ ለማስፈጸም መጥተው ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ አቶ ፍሰሐ ሰለሞን ናቸው። በማእከሉ ተቋማት በሚሰጡት ፈጣን አገልግሎት መደሰታቸውን ጠቁመው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመልክተዋል።
ስፖርት
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ልደታ ክፍለ ከተማ እና ቦሌ ክፍለ ከተማ ነጥብ ተጋሩ
Mar 6, 2026 34
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ልደታ ክፍለ ከተማ እና ቦሌ ክፍለ ከተማ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። በኤፍኤ ካፕ ሊቨርፑል ከዎልቭስ ጋር ይጫወታል በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሰብለወንጌል ወዳጆ እና ይታገሱ ተገኝወርቅ ለልደታ ክፍለ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ቃልኪዳን ሸዋነህ እና ዳሳሽ ሰውአገኝ የቦሌ ክፍለ ከተማን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። የልደታ ክፍለ ከተማዋ ሜሮን አበበ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። ውጤቱን ተከትሎ ልደታ ክፍለ ከተማ በ15 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ቦሌ ክፍለ ከተማ በ30 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ይጫወታል
Mar 6, 2026 77
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል። ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። በኤፍኤ ካፕ ሊቨርፑል ከዎልቭስ ጋር ይጫወታል ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች መካከል ስድስቱን ሲያሸንፍ ዘጠኝ ጊዜ ተሸንፏል። አንድ ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። 15 ግቦችን በ16ቱ ጨዋታዎች ላይ ሲያስቆጥር 24 ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ19 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሊጉ ባከናወናቸው 16 ጨዋታዎች 14ቱን አሸንፏል። አንድ ጊዜ ሲሸነፍ በተመሳሳይ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። 36 ግቦችን በጨዋታዎቹ ላይ ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ሰባት ጎሎች ተቆጥረውበታል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ43 ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱም ቡድኖች ተከታታይ ድላቸውን ለማስመዝገብ ይጫወታሉ። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካሸነፈ የሊጉን መሪነት ያጠናክራል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ይርጋጨፌ ቡና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አዲስ አዳጊው ይርጋጨፌ ቡና በሊጉ ባከናወናቸው ዘጠኝ ጨዋታዎች ሁለቱን ሲያሸንፍ ዘጠኝ ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 7 ግቦችን ሲያስቆጥር 22 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ይርጋጨፌ ቡና በ11 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሊጉ ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ13ቱ አሸንፎ በአንዱ ተሸንፎ ሁለት ጊዜ አቻ ወጥቷል። ቡድኑ 42 ግቦችን ሲያስቆጥር አምስት ጎሎች አስተናግዷል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ41 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ልደታ ክፍለ ከተማ ከቦሌ ክፍለ ከተማ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ልደታ ክፍለ ከተማ በ14 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ቦሌ ክፍለ ከተማ በ29 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ለይ ተቀምጧል። ሁለቱም ቡድኖች በድል ጉዟቸው ለመቀጠል የሚያደርጉት ጨዋታ ተመጣጣኝ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት እስከ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የኢትዮ ኤሌክትሪኳ ዳግማዊት ሰለሞን በ18 ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራች ነው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ ረድኤት አስረሳኸኝ በ12 ግቦች ቀጣዩን ደረጃ ይዛለች።
በኤፍኤ ካፕ ሊቨርፑል ከዎልቭስ ጋር ይጫወታል
Mar 6, 2026 87
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ኤፍኤ ካፕ አምስተኛ ዙር መርሐ-ግብር ዛሬ ይጀመራል። በሞልኒው ስታዲየም ዎልቭስ ከሊቨርፑል ምሽት አምስት ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። ዎልቭስ በአራተኛው ዙር ግሪምስቢ ታውንን፣ ሊቨርፑል ብራይተንን አሸንፈዋል። ክለቦቹ በኤፍኤ ካፕ ሲገናኙ የዛሬው ለስድስተኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው አምስት ጨዋታዎች ዎልቭስ ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ ሊቨርፑል አንድ ጊዜ ድል ቀንቶታል። በቀሪ አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። እ.አ.አ 2023 በውድድሩ ላይ ለመጨረሻ ጊዜ በተገናኙበት ጨዋታ ሊቨርፑል በድምር ውጤት በማሸነፍ ወደ አራተኛው ዙር ማለፉ የሚታወስ ነው። ዎልቭስ ኤፍኤ ካፕን አራተኛ ጊዜ፣ ሊቨርፑል ስምንት ጊዜ ዋንጫውን አንስተዋል። ባለሜዳው ዎልቭስ ለመጨረሻ ጊዜ ውድድሩን ያሸነፈው እ.አ.አ በ1960 ነው። ሊቨርፑል የመጨረሻውን ዋንጫ ያነሳው እ.አ.አ በ2022 መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። ሁለቱ ቡድኖች በሳምንቱ አጋማሽ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 29ኛ ሳምንት ባደረጉት ጨዋታ ዎልቭስ በሜዳው 2 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። በቀናት ልዩነት በኤፍኤ ካፑ ይገናኛሉ። የ32 ዓመቱ ፋራይ ሃላም ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የኤፍኤ ካፕ የአምስተኛ ዙር መርሐ ግብር እስከ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ጨዋታውን የሚያሸንፉ ክለቦች ወደ ሩብ ፍጻሜ ያልፋሉ። ኤፍኤ ካፕ 155 ዓመታትን ያስቆጠረ አንጋፋ የክለቦች ውድድር ነው።
ክሪስታል ፓላስ ቶተንሃም ሆትስፐርን አሸነፈ
Mar 6, 2026 65
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 29ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሐ- ግብር ክሪስታል ፓላስ ቶተንሃም ሆትስፐርስን 3 ለ 1 አሸንፏል። ትናንት ማምሻውን በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየሞ በተካሄደው ጨዋታ ኢስማይላ ሳር በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ሁለት ግቦች ሲያስቆጥር ጆርዳን ስትራንድ ላርሰን ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ዶምኒክ ሶላንኬ ለስፐርስ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። የቶተንሃሙ ተከላካይ ሚኪ ቫን ዴቬን በ38ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ወጥቷል። የተጫዋቹ ከሜዳ መውጣት በቶተንሃም የጨዋታ እንቅስቃሴ ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። በቡድናቸው ብቃት ያልተደሰቱት የቶተንሃም ደጋፊዎች ጨዋታውን አቋርጠው ከሜዳ ወጥተዋል። በሊጉ 14ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ29 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዟል። የሰሜን ለንደኑ ክለብ ባለፉት 11 የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። አዲሱ አሰልጣኝ ኢጎር ቱዶር በሶሶት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ተሸንፏል። በሊጉ 10ኛ ድሉን ያስመዘገበው ክሪስታል ፓላስ በበኩሉ በ38 ነጥብ ደረጃውን ከ14ኛ ወደ 13ኛ ከፍ አድርጓል።
አካባቢ ጥበቃ
በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ ነው
Mar 6, 2026 61
ጋምቤላ ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች በቀጣዮቹ ሶስት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ መሆኑን በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋምቤላ ክልል ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አስታወቀ። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል በኢንስቲትዩቱ የጋምቤላ ክልል የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋሁን ዓለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ወይና ደጋማ አካባቢ በቀጣይ ወራት የሚኖረው የበልግ ዝናብ ለእርሻ ስራ ተስማሚ ነው። በክልሉ ወይና ደጋማ የአየር ፀባይ ያለው የማጃንግ ዞን በቀጣዩቹ ሶስት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለእርሻ ስራና ለእንስሳት ግጦሽ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር የአየር ትንበያ መረጃ ያመለክታል ብለዋል። በተለይም በዞኑ ቀድመው ለሚዘሩ የሰብል ዓይነቶችና ለመኸር እርሻ ስራ ዝግጅት በቂ የዝናብ ስርጭት እንደሚኖር መተንበዩን አመላክተዋል ። በሌላ በኩል ደግሞ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት በክልሉ ቆላማ አካባቢዎች ጠንከር ያለ የሙቀት መጠን እንደሚኖር የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጸዋል። በመሆኑም የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር የውሃ መጠን መቀነስ ሊኖር ስለሚችል ህብረተሰቡ ውሃን በአግባቡ መጠቀም እንዳለበት ምክር ሃሳብ ሰጥተዋል። እንዲሁም ከሙቀቱ መጨመር ጋር ተያይዞ በሰዎች ላይ የቆዳ ሽፍታ ሊከሰት ስለሚችል ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል
Mar 5, 2026 83
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አስከፊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም ገለጸ። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ተፈፃሚነት ያላት ቁርጠኝነት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንዳስቻላት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ተቋማዊ ልማት አማካሪ መንሱር ደሴ ገልጸዋል። ከየካቲት 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የአውደ ጥናት የምክክር መድረክ ተጠናቋል። በአውደ ጥናቱ ማጠናቀቂያ ላይ የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የአፍሪካ አስተባባሪ ጆንኪ ቴኑ፤ የአካባቢና የሥነ-ምኅዳር ደኅነንት ለማስጠበቅ ትብብርን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል። አውደ ጥናቱም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ተግባራዊ የተደረጉ መርሃ ግብሮችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ስኬታማ የልምድ ልውውጥና ግብዓት እንደተገኘበት ገልጸዋል። በፖሊሲዎችና የትኩረት መስኮች የተደረገው ውይይትም የዕውቀት ሽግግር የተደረገበት መሆኑን ተናግረዋል። ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የመንግሥታቱን ድርጅት የአየር ንብረት ስምምነት መነሻ በማድረግ ለተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ እያቀረበ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሀገራትም የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አስከፊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአካባቢ ጥበቃ ተቋም ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚያግዝ አረጋግጠዋል። በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ተቋማዊ ልማት አማካሪ መንሱር ደሴ በበኩላቸው፤ በአውደ ጥናቱ ከ14 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 150 ሙያተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ትግበራ ያላት ቁርጠኝነት በልማት አቅጣጫዎቿ ላይ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን አስረድተዋል። በአውደ ጥናቱም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም በተደረገ ድጋፍ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት መቅረባቸውን ተናግረዋል። ከሀምሌ ወር ጀምሮ ለአራት ዓመታት የሚተገበረው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም መርሃ ግብርም ከኢትዮጵያ የልማት አቅጣጫዎች ጋር ተጣጥመው እንደሚተገበሩ አንስተዋል።
በምስራቅ ሸዋ ዞን የአካባቢውን ሥነ ምሕዳር መሠረት ያደረጉ ችግኞች እየተዘጋጁ ነው
Mar 4, 2026 186
አዳማ ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የአካባቢውን ሥነ ምሕዳር መሠረት ያደረጉና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን የማፍላት ስራ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በምስራቅ ቦረና ዞን የእንስሳት መኖ እጥረት እንዳያጋጥም የመኖ ልማት ስራ ከተፋሰስ ጥበቃ ጋር ተቀናጅቶ እየተከናወነ ነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ሃገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ሐምሌ 2011 ዓ.ም መጀመሩ ይታወቃል። በምስራቅ ሸዋ ዞን ግብርና የጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዞኑ 11 ወረዳዎች ባሉ የችግኝ ማፊያ ጣቢያዎች ለመጪው ክረምት የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ተጀምሯል። ችግኝ ጣቢያዎቹ ለአረንጓዴ አሻራ ዘመቻው የተለያየ ዝርያ ያላቸው ችግኞችን አፍልቶ በማቅረብ ረገድ እያበረከቱ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን አስታውሰዋል። ዘንድሮም ለማዘጋጀት ከታቀደው ከ284 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ውስጥም 241 ነጥብ 4 ሚሊዮን ችግኞችን የማፍላት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። ቀሪ ችግኞችን የማፍላት ሥራም እስከ መጪው ግንቦት ወር ድረስ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በችግኝ ዝግጅቱም በአብዛኛው የአየር ንብረት መዛባትን ለመከላከል ለሚያገለግሉ የደን እና ጥምር ደን ዝርያዎች ትኩረት የተሰጠ መሆኑን አስረድተዋል። በተጨማሪም ለአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን የሚያስገኙና እና ለምግብነት የሚውሉ 26 ነጥብ 7 ሚሊዮን የፍራፍሬ ችግኞችን ያካተተ የዘር ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል። የዘንድሮ ዓመት የችግኝ ተከላ የአካባቢውን ሥነ ምሕዳር መሠረት በማድረግ የሚከናወን መሆኑን ጠቁመው በዞኑ ባለፉት ዓመታት ከተተከሉ ችግኞች ከ85 በመቶ በላይ መጽደቃቸውን አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅትም የተተከሉ ችግኞችን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ የመጠበቅና የመንከባከብ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ነው ያረጋገጡት። በዘንድሮው ዓመት በዘርፉ የተቀመጠውን እቅድ ለማሳካትም የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ተቆፍረው መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል
Mar 3, 2026 189
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት እንደሚጠበቅባቸው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ገለጸ። "በምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የሚቋቋም ግብርናን ማስፋፋት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ቀጣናዊ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በኢጋድ፣ የዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ፣ የሥርዓተ ምግብ ፕሮግራም ለምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ፣ የደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምርና ልማት ማስተባበሪያ ትብብር በተዘጋጀው መድረክም የግብርና ማሻሻያ ምክረ ሀሳቦችን እንደሚያፈልቅ ይጠበቃል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ተወካይ ዳህር ኤልሚ፤ በአየር ንብረትና በሥነ-ምኅዳር ደኅንነት የሚከሰት ለውጥ የግብርና ምርታማነት ላይ ጫና እያሳደረ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለው የአፈር መራቆት፣ ድርቅ፣ ጎርፍ፣ ዝናብ እጥረትና በርሃማነት የምስራቅ አፍሪካ የግብርና ምርታማነትና የምግብ ፍጆታ ላይ አሉታዊ ጫና እንደሚያሳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የቀጣናው ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት ለመገንባት የቴክኖሎጂ፣ የግብዓትና የመረጃ ትንተና አቅም መገንባት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣንም የቀጣናውን ሀገራት የግብርና ምርታማነት የሚያሻሽል የአየር ሁኔታ የመረጃ ትንተና ተደራሽ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢኒስቲትዩት የተፈጥሮ ሃብትና የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም ፕሮግራም ዳይሬክተር አወቀ ሙሉዓለም በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ሥርዓት ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችም የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ የአርሶና አርብቶ አደሩን የግብርና ምርታማነት እያሳደገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን፤ የግብርና ምርታማነት የሚያዘምኑ የፋይናንስና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በማስፋት የቀጣናው ሀገራት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር የኢጋድና የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦዌን በበኩላቸው፤ የግብርና ምርታማነትን ማረጋገጥ ለአፍሪካ ዕድገትና ብልጽግና ወሳኝ ነው ብለዋል። የቀጣናውንና አፍሪካን የግብርና ሥርዓት ለማዘመን በሚደረገው ጥረትም የኒውዝላንድ መንግስትና የልማት አጋሮች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች፣ ፖለሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮችና ተመራማሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በሰላምና ደኅንነት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Mar 5, 2026 78
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢጋድ የሰላም እና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ውይይቱን ያደረጉት የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁን (ዶ/ር) በመወከል ነው። ውይይቱ ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም፣ ደኅንነት እና መረጋጋት ላይ ያላቸውን የጋራ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው። ሁለቱ ወገኖች የጋራ የተግባር ምላሽ ለመስጠት እና ስትራቴጂካዊ ትብብራቸውን ለማጎልበት ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የመንግሥታቱ ድርጅትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ ይገባል
Mar 4, 2026 188
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ እንደሚገባ ተገለጸ። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከጃፓን ኤምባሲ ጋር በመሆን የተባበሩት መንግሥታት ሪፎርም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል። የመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩ ቢሆኑም በተቋማዊ አወቃቀር ሥርዓት ላይ አፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ያገለሉ ናቸው። የአማኒ አፍሪካ ዳይሬክተር ሰለሞን አየለ ደርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት መዋቅር የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃ ሊወስድ ይገባል። በተቋማቱ የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥም ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ተከታታይ ሥራ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። የአህጉሪቱ አባል ሀገራትና ከሌሎች ሀገራት ጋር ትብብርን በማጠናከር የአፍሪካን የዓለምአቀፍ ተቋማት ፍትሐዊ ውክልና ማስከበር የሚስችል መዋቅራዊ የሪፎርም እርምጃ እንዲወሰድ መስራት ይገባል ብለዋል። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በአፍሪካ ሕብረትና የአፍሪካ ዳያስፖራ ጉዳዮች ላይ በጥናትና ምርምር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የጋና አምባሳደር ሮበርት አፍሪይ(ዶ/ር)፤ አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ተቋማት ያቀረበችው ፍትሐዊ የውክልና ጥያቄ ችላ በመባሉ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ የሌላት ብቸኛ አህጉር አድርጓታል ብለዋል። ለዚህም የመንግስታቱ ድርጅት አፍሪካ በተሸከመችው የጸጥታው ምክር ቤት የሥራ ጫና ልክ ውክልና የሚያስገኛትን የሪፎርም እምርጃ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። በአፍሪካ ሕብረት የጃፓን ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኖቦሩ ሴኪጉቺ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በመንግስታቱ የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ላይ ፍትሐዊ ውክልና ሊሰጣት ይገባል ብለዋል። ጃፓንም አፍሪካ በመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የሚኖራትን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። ጃፓንና የጂ-4 አባል ሀገራት የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡም አስታውቀዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2024 በጸደቀው "የወደፊት ስምምነት" ላይ የጸጥታው ምክር ቤት መዋቅራዊ የማሻሻያ እርምጃ ለመወሰድ የተቀመጠው አቅጣጫ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቀጣናዊ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Mar 1, 2026 156
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ እያሳደረ ባለው ከፍተኛ ተጽእኖ ምክንያት የቀጣናው የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እና የዜጎች የኑሮ መሰረት አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብ ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል።
የኢጋድ እና ተመድ ትብብር ለቀጣናዊ ሰላም
Feb 26, 2026 188
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት ያላቸውን የጋራ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የኢጋድ የደቡብ ሱዳን ልዩ ልዑክ አምባሳደር ሙሳ ጃማ አሊ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ጉዋንግ ኮንግ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። ልዩ ልዑኮቹ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት በተለይም በደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቅርቡ የአፍሪካ ህብረት የአምስት አባል ሀገራት ኮሚቴ (AU C5) እና ኢጋድ ያደረጉት የጋራ ጉባኤ የተገኙ ውጤቶች ላይም መክረዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ሰላም፣ መረጋጋት እና ቀጣናዊ ትብብር እውን እንዲሆን ያላቸውን ቅንጅት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 191
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 252
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 264
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 705
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 284
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 390
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1126
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1110
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3604
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2406
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8204
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6687
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 393
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 374
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።