ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ጨፌው በክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና ውስንነቶች ላይ በስፋት ይወያያል
Feb 13, 2026 8
አዳማ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የጨፌ ኦሮሚያ በክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና ውስንነቶች ላይ በስፋት እንደሚወያይ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን ገለፁ። የጨፌ ኦሮሚያ 6ኛ የስራ ዘመን 5ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ጉባኤ ነገ በአዳማ ገልመ ጨፌ መካሄድ ይጀምራል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን ጉባኤውን በማስመልከት መግለጫ በሰጡበት ወቅት ጨፌው በክልሉ ያለፉት ስድስት ወራት የመንግስት የስራ አፈጻጸም ዕቅድ ክንውን ላይ ውይይት ያደርጋል ብለዋል። በተለይ በግማሽ ዓመቱ የክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና ውስንነቶች ላይ ይወያያል ነው ያሉት። በተጨማሪም የጨፌው አባላትና ቋሚ ኮሚቴዎች በወረዳዎች፣ በከተሞችና በዞኖች ባደረጉት የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም በመስክ ምልከታ የተገኙ ሪፖርቶች ለጉባኤው ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸውም ጠቁመዋል። ጉባኤው የዳኞች ሹመትን ጨምሮ የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት በመወያየት ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክተዋል።
ለግብርና ልማት ሥራ ውጤታማነት በተሰጠው ትኩረት ተጠቃሚነታችን እያደገ ነው -አርሶ አደሮች
Feb 13, 2026 6
ሚዛን አማን ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦መንግሥት ለግብርና ልማት ሥራ ውጤታማነት በሰጠው ትኩረት ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ። የወረዳው አርሶ አደሮች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትና የሌማት ትሩፋት መርሀግብሮችን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ኢኒሼቲቮች የኢኮኖሚ አማራጮችን በማስፋት ገቢያቸውን እያሳደጉ ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል አርሶ አደር ጣሃ ሐቢብ እንዳሉት በቆሎ፣ ማሽላ፣ ቡና፣ ቁንዶ በርበሬ፣ እርድና ዝንጅብል በማልማት ኑሯቸውን እየመሩ ነው። ከግብርና ልማት ሥራቸውም ከዚህ ቀደም ከሚያገኙት የተሻለ ምርት በማምረት ገቢያቸውን እያሰደጉ መምጣታቸውን ተናግረዋል። ምርቶችን በጥራት አምርተን የልፋታችንን ያህል ውጤት እንድናገኝ በመንግስት በኩል የተሻሻለ ዝርያና የግብርና ግብአት አቅርቦት ድጋፍ ይደረግልናል ያሉት አርሶ አደር ጣሃ፣ የመንግስት እገዛና ክትትል ለስኬታማነታቸው አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የሌማት ትሩፋት መርሀግብር፣ የገጠር ኮሪደር እና መሰል የመንግሥት የልማት ኢኒሼቲቮች የኢኮኖሚ ምንጭ በመሆን የአርሶ አደሩን ሕይወት እያሻሻሉ መሆኑንም አክለዋል። የበጋ መስኖ ስንዴ፣ የሩዝና መሰል የሰብል ልማት ሥራዎች ተጠናክረው ከቀጠሉ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ ናቸው ያሉት ደግሞ አርሶ አደር አያሌው ኃይሉ ናቸው። በተለይ በቡና እና በቅመማ ቅመም ምርት የተሻለ ገቢ በማግኘት ለውጥ እንዲያመጡ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው ነው የገለጹት። የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን በምርምር ተቋማት በኩል መንግሥት እያቀረበ በመሆኑ በማሳቸው አላምደው ምርታማነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን የገለጹት ደግሞ አርሶ አደር ታምራት እረና ተናግረዋል። ሩዝን ጨምሮ በአካባቢው ያልተለመዱ ሰብሎችን በማልማት ውጤታማ መሆን እንደተቻለ ጠቅሰው መንግሥት ለግብርና ልማት የሰጠው ትኩረት ምርታማነታችንን የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል። የእርሻ ሥራቸው ውጤታማ እየሆነ በመምጣቱ ምርታቸውን ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉና ጥሪት እያፈሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሸካ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ አዕምሮ ደሳለኝ፤ በዞኑ የግብርና ኢኒሺየቲቭ ሥራዎች በአርሶ አደሮች ማሳ እንዲተገበሩ የተሰራው ሥራ ውጤት እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም በ10 አርሶ አደሮች ማሳ ከአራት ዓመት በፊት የተጀመረው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ዘንድሮ ከ2ሺህ 500 በሚበልጡ አርሶ አደሮች ማሳ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። በተመሳሳይ በ300 ሄክታር ማሳ ላይ የተጀመረው የሩዝ ልማት ዘንድሮ ወደ 3ሺህ 200 ሄክታር ማደጉን ገልጸው፣ በሌማት ትሩፋትም እየመጣ ያለው ውጤት እንዲጠናከር በመምሪያው በኩል ድጋፍና ክትትሉ መጠናከሩን ጠቁመዋል።
በጤና ዘርፍ የሚደረግ ኢንቨስትመንት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ ትልቅ መሠረት ይጥላል
Feb 13, 2026 10
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ በጤና ዘርፍ ላይ የሚደርግ ኢንቨስትመንት የሀገርን ምርታማነት ከማሳደግ ባለፈ ለዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ መሠረት መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ ገለጹ። ሚኒስትር ዴኤታው ይህንን የገለጹት “በኢትዮጵያ የወደፊት ዕድል ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፤ ከጤና ወጪ ወደ ጤና ኢንቨስትመንት” በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀው የዘላቂ ጤና ፋይናንስ የንቅናቄ ወርክሾፕ ላይ ነው። ዶክተር ደረጀ ድጉማ በዚሁ ወቅት፤ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ የሚመድበው በጀት ጤናማና አምራች ዜጋን በመፍጠር በኩል የላቀ ድርሻ አለው ብለዋል። እስካሁን ባለው ሂደትም በርካታ የጤና ተቋማት ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸውና ዘመናዊና ወሳኝ የሕክምና መሣሪያዎችን የማሟላት ሥራ፣ ብቁና በቂ የሰው ኃይል የማፍራት ተግባር መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ መንግሥት በቀጣይ የዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ ዘላቂ የፋይናንስ ሥርዓት መዘርጋትን እንደ ቀዳሚ ተግባር መያዙንም ጠቅሰዋል፡፡ የጤና ፋይናንስ ሥርዓቱ አስተማማኝ ወደ ሆኑ የሀገር በቀል የፋይናንስ ምንጮች መሸጋገር እንዳለበትም ነው የገለጹት፡፡ ይህንን ግብ ለማሳካትም በርካታ ተግባራት እንደሚከናወኑ ጠቁመው የፋይናንስ ምንጮችን በሀገር ውስጥ አቅም ማጠናከር፣ የጤና መድህን ሽፋንን በስፋት ማዳረስ እንዲሁም የግል ባለሀብቶችና አጋር አካላት በዘርፉ እንዲሳተፉ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ጤናማ ዜጋ ለሀገር እድገት ያለው ሚና የማይተካ መሆኑን በመጥቀስ፡፡ በመድረኩ የተገኙት በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት(WHO) የስትራቴጂክ ጤና ፖሊሲና ፕላን አስተባባሪ ዶክተር ቢጆይ ፒ. ናምቢያር፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ዘርፉን ለማዘመን እየከወናቸው ያሉ ተግባራት የሚደነቁ ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ የራሷን ዘላቂ የጤና ፋይናንስ ለማረጋገጥ የጀመረችው እንቅስቃሴ ወቅታዊና ስትራቴጂካዊ መሆኑንም ጨምረው ጠቁመዋል፡፡
የአገልግሎት አሰጣጥ መዘመንና የመሰረተ ልማት መሟላት ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እያደረጋት ነው
Feb 13, 2026 16
ኮምቦልቻ ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦የአገልግሎት አሰጣጥ መዘመንና የመሰረተ ልማት መሟላት ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እያደረጋት መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) ገለጹ። በኮሚሽኑ የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈጻሚዎች የጋራ የምክክር መድረክ በኮምቦልቻ እየተካሄደ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር)፤የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን በማሟላትና አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን መሳብ ተችሏል ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት በዘርፉ ላይ ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን ጠቅሰው፤ ከ2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ካፒታል ያላቸው የውጭ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰሳቸውን ተናግረዋል። ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ20 በመቶ ጭማሬ አለው ብለዋል። አክለውም በፌዴራል ደረጃ ለ245 የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል። ባለፉት ስድስት ወራት የቻይና፣ የህንድ፣ የአሜሪካ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና የሌሎች አገራት ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት ፍቃድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። የአገልግሎት አሰጣጡ መዘመንና የመሰረተ ልማት መሟላት ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እያደረጋት መሆኑንም ኮሚሽነሩ አመልክተዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የክልሉን ሰላም በማጽናት የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ ናቸው ብለዋል። ባለፉት ስድስት ወራት በክልሉ ከፍተኛ ሃብት ላስመዘገቡ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ጠቁመው፣ የመሰረት ልማቱንና አገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል ወደ ሥራ እንዲገቡም እየተደረገ ነው ብለዋል።
ሁለተኛው የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Feb 13, 2026 25
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/ 2018(ኢዜአ)፦ ሁለተኛው የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል። ጉባኤው የጣሊያን-አፍሪካ ግንኙነት በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብሮች ይበልጥ እንዲጠናከር የሚያደርግ ነው፡፡ ጉባኤው በአዲስ አበባ መካሔዱ ኢትዮጵያ አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር ያላትን አቅም እንደሚያሳይ ተገልጿል። ኢትዮጵያ 39ኛውን የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ እና የጣሊያን አፍሪካ ጉባዔን ለማስተናገድ ተዘጋጅታ እንግዶቿን እየተቀበለች ትገኛለች። የተለያዩ ሀገራት መሪዎችና የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ የተቋማት ኃላፊዎች አዲስ አበባ ይገኛሉ። የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው ነው።
ፖለቲካ
ጨፌው በክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና ውስንነቶች ላይ በስፋት ይወያያል
Feb 13, 2026 8
አዳማ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የጨፌ ኦሮሚያ በክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና ውስንነቶች ላይ በስፋት እንደሚወያይ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን ገለፁ። የጨፌ ኦሮሚያ 6ኛ የስራ ዘመን 5ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ጉባኤ ነገ በአዳማ ገልመ ጨፌ መካሄድ ይጀምራል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን ጉባኤውን በማስመልከት መግለጫ በሰጡበት ወቅት ጨፌው በክልሉ ያለፉት ስድስት ወራት የመንግስት የስራ አፈጻጸም ዕቅድ ክንውን ላይ ውይይት ያደርጋል ብለዋል። በተለይ በግማሽ ዓመቱ የክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና ውስንነቶች ላይ ይወያያል ነው ያሉት። በተጨማሪም የጨፌው አባላትና ቋሚ ኮሚቴዎች በወረዳዎች፣ በከተሞችና በዞኖች ባደረጉት የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም በመስክ ምልከታ የተገኙ ሪፖርቶች ለጉባኤው ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸውም ጠቁመዋል። ጉባኤው የዳኞች ሹመትን ጨምሮ የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት በመወያየት ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክተዋል።
ሁለተኛው የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Feb 13, 2026 25
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/ 2018(ኢዜአ)፦ ሁለተኛው የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል። ጉባኤው የጣሊያን-አፍሪካ ግንኙነት በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብሮች ይበልጥ እንዲጠናከር የሚያደርግ ነው፡፡ ጉባኤው በአዲስ አበባ መካሔዱ ኢትዮጵያ አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር ያላትን አቅም እንደሚያሳይ ተገልጿል። ኢትዮጵያ 39ኛውን የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ እና የጣሊያን አፍሪካ ጉባዔን ለማስተናገድ ተዘጋጅታ እንግዶቿን እየተቀበለች ትገኛለች። የተለያዩ ሀገራት መሪዎችና የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ የተቋማት ኃላፊዎች አዲስ አበባ ይገኛሉ። የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው ነው።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አንድነትና ትብብር የምታበረክተው አስተዋጽኦ የአህጉሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለማፋጠን ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል
Feb 13, 2026 21
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አንድነትና ትብብር የምታበረክተው አስተዋጽኦ የአህጉሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርና ውህደት ለማፋጠን ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ሲሉ የኢኳቶሪያል ጊኒ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ማሪ-ክሩዝ ኢቩና አንዴሜ ገለጹ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካውያን የችግር ጊዜ ደራሽ፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ማስተሳሰሪያ ድልድይ መሆኑንም ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት 48ኛው የሥራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ትናንትና ከትናንት በስቲያ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ የሕብረቱ ዋና መስሪያ ቤት ሲካሄድ ቆይቶ ትናንት ተጠናቋል። 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔም "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ ነገና ከነገ በስትያ ይካሄዳል። የጉባኤው ተሳታፊ የኢኳቶሪያል ጊኒ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ማሪ-ክሩዝ ኢቩና አንዴሜ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ለደቡብ ደቡብ ትብብር መጎልበት ቁርጠኛ አቋም ያላት ሀገር ናት። ኢትዮጵያ በአህጉራዊ አንድነት ላይ ያላት ቁርጠኛ አቋም የደቡብ-ደቡብ ትብብርን በማጠናከር ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን ለማፋጠን ከፍተኛ አቅም እየሆነች እንደምትገኝም ገልጸዋል። ለአብነትም ከዓመታት በፊት የተከሰተው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥርጭትን ለመከላከል በተደረገው አህጉራዊ ጥረት ኢትዮጵያ የሕክምና ቁሳቁሶችን ለአፍሪካ ሀገራት በማዳረስ አስደናቂ አጋርነቷን በተግባር አሳይታለች ብለዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድም የወረርሽኝ መከላከያ መድኃኒትና ቁሳቁሶችን ለአፍሪካውያን በማዳረስ የችግር ጊዜ ደራሽ መሆኑን በተግባር ያስመሰከር ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የገነባው የተደራሽነት አድማስም የአፍሪካ ሀገራትን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር በማጠናከር አይነተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ኢትዮጵያ መሠረተ ልማቷን ለአፍሪካ እያጋራች መሆኑን ያሳያል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ በምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ውህደትም የመሪነት ሚና እየተወጣች ትገኛለች ነው ያሉት። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ መሆኗ በአህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ግንባር ቀደም ተዋናይነቷን በማጉላት የአፍሪካውያን አስተሳሳሪ ዋልታ እንድትሆን ማስቻሉን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤን በየዓመቱ በስኬት በማስተናገድ አህጉራዊ ትብብሮችን ለማጎልበት ትልቅ አቅም እየሆነች እንደምትገኝም ነው ጨምረው የገለጹት። ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አንድነትና ትብብር የምታበረክተው አስተዋጽኦ የአህጉሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርና ውህደት ለማፋጠን ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አብራርተዋል።
ምርጫው ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የምክር ቤት አባላት ሚና ወሳኝ ነው
Feb 13, 2026 43
አርባ ምንጭ ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የምክር ቤት አባላት ሚና ወሳኝ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አፈ- ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ አመለከቱ። የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአርባ ምንጭ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል። ዋና አፈ ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ በመክፈቻው መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ጠቅላላ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የምክር ቤት አባላት ሚና ሰፊ ነው ብለዋል። የለውጡ መንግስት የሀገራችንን ኋላ ቀር የፖለቲካ ልምምድ በመቀየር ሰው ተኮር የፖለቲካ ምህዳር በመትከል ሁለንተናዊ ልማት እያረጋገጠ ይገኛል ነው ያሉት። የጋራ ሀገርና የጋራ ሃሳብ ላይ የተመሠረተ ገዢ ትርክት በመገንባት የህዝቡን አንድነትና አብሮነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ምክር ቤቶች የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተምሳሌት እንደመሆናቸው መጠን የህዝቡ የልማት፣ የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱና የልማት ተጠቃሚነት ይበልጥ እንዲረጋገጥ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ አመልክተዋል። በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካዊ ዘርፎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ዋና አፈ ጉባኤው በንግግራቸው አንስተዋል። በክልሉ ያለውን ዕምቅ የግብርና አቅም ለመጠቀም የኩታ ገጠም እና የሜካናይዜሽን ልማትን ለማስፋፋት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ከልማዳዊ አሠራር በመውጣት ገበያን የሚያረጋጋ ምርት እንዲገኝ እያደረገ ስለመሆኑ ተናግረዋል። በመሠረተ ልማት፣ በትምህርትና በሌሎችም ዘርፎች ፍትሃዊ ተደራሽነትን በማረጋገጥ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ሰፊ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል። አቶ አለማየሁ፤ በክልሉ የተከሰተውን የማርበርግ ቫይረስ በህዝብና በአመራሩ የተቀናጀ ተግባር መቆጣጠር መቻሉንም አመልክተዋል። ክልሉን የሰላም፣ የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ በተደረጉ ጥረቶች በሁሉም አካባቢ ለውጥ ተመዝግቧል ብለዋል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው መደበኛ ጉባኤም የክልሉ መንግስት የ2018 ዓ.ም ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ማድመጥና ማጽደቅን ጨምሮ ልዩ ልዩ አዋጆችና ደንቦች እንዲሁም ሹመቶች እንደሚፀድቁም ይጠበቃል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገር የምታሸንፍበት እንዲሆን በቅንጅት እንሰራለን-የተፎካካሪ ፓርቲዎች
Feb 13, 2026 37
ባህርዳር፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገር የምታሸንፍበት እንዲሆን ቅንጅታቸውን የበለጠ እንደሚያጠናክሩ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ገለጹ። ''ለሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በጋራ እንቁም'' በሚል መሪ ሃሳብ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተፎካካሪ ፖርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መድረክ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ ተስፋሁን አለምነህ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና አሳታፊ እንዲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው። ምርጫው ሕግና አሰራርን ተከትሎ ሁሉም ፓርቲዎች በነፃነት የሚሳተፋበትና በሕዝብ ዘንድ አመኔታ ያተረፈ እንዲሆን ትብብርን የበለጠ ማጠናከር ይገባል ብለዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ስልጡን ፖለቲካን በማራመድ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። በምርጫ አሸናፊና ተሸናፊ መኖሩ ተፈጥሯዊ ቢሆንም በፋክክር ሂደቱ እኩል በመሳተፍ በምርጫው ሀገር እንድታሸንፍ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራሩን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምክር ቤቱ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊና አሳታፊ እንዲሆን ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። በምርጫ ሂደቱ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ መፍታት ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችና ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቀቀ
Feb 13, 2026 63
ታርጫ ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችን፣ ተጨማሪ በጀትና ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቀቀ። የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀን ውሎው የተለያዩ አዋጆችን፣ ተጨማሪ በጀትና ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቋል። በጉባኤውም ወደ ከተማ የተካለሉ ቀበሌዎችን የተመለከተ ሞሽን የቀረበ ሲሆን ይህም በየመዋቅሩ የሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለህዝቡ ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል። በዚህም መሰረት ከሸካና ቤንች ሸኮ ዞኖች 10 ቀበሌዎች ሙሉ በሙሉና በከፊል ወደ ቴፒና ሸኮ ዞኖች እንዲካለሉ በቀረበው የድጋፍ ሞሽን ላይ የምክር ቤቱ አባላት ውይይት አካሄደዋል። ሞሽኑን በተመለከተ ጥያቄና አስተያየቶች ቀርበው ምላሽ ከተሰጠበት በኋላ በአዋጅ ቁጥር 3/2018 ሞሽኑ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል። እንዲሁም ለኢኮኖሚው እገዛ ለማድረግ የሚያስችል የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ ደንብ ቀርቦ ውይይት ከተደረገ በኋላ በአዋጅ ቁጥር 49/2018 በሚል በሙሉ ድምፅ ሊፀድቅ ችሏል። በክልሉ ምክር ቤት ተጨማሪ የበጀት ረቂቅ ላይ ውይይት በማድረግ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የሚውል 657 ሚሊዮን 600 ሺህ ብር ተጨማሪ በጀትን ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል።ምክር ቤቱ በሁለተኛ ቀን ውሎውም ሌሎች አዋጆችን ማፅደቁም ተመልክቷል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ ለተለያዩ የሥራ ክፍሎች የቀረቡ እጩዎችን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል። በዚህም መሰረት፤- 1. አቶ ንጉሴ ወልደጊዮርጊስ፤ የክልሉ ሰው ሀብትና ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ 2. ረዳት ፕሮፌሰር ዘመድኩን ሰለሞን ፤የኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ ኃላፊ 3. አቶ መቱ አኮ፤ የክልሉ ቆላማና እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ቢሮ ኃላፊ 5. አቶ ታሪኩ አካሉ፤ የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም ሌሎች ሽግሽግ የተደረገባቸው ኃላፊዎች ዝርዝር ቀርቦ በምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል። ተሿሚዎችም በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል ።
ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የሲቪክ ማህበራት ዝግጅት ምን ይመስላል?
Feb 13, 2026 42
ቦንጋ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ ዘንድሮው በሚከናወነው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት እንዲሁም ለዜጎች የነቃ ተሳትፎ የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚገኙ የሲቪክ ማህበራት ድርጅቶች ገለጹ። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሮ የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎቻቸውን እያስመዘገቡ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወጣው መርሃ ግብር እንደሚያመለክተው የመራጮች ምዝገባ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀምር ይሆናል። በዚህ የምርጫ ሂደት በተለይም የሲቪክ ማህበራት ግንዛቤ በመፍጠርና በታዛቢነት ጭምር በመሳተፍ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት መጎልበት የድርሻቸውን አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ይሆናል። ከዚህ አንፃር ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የሲቪክ ማህበራት ዝግጅት ምን ይመስላል? ሲል የኢዜአ ሪፖርተር በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚገኙ የሲቪክ ማህበራት ድርጅቶችን አነጋግሯል። የሲቪክ ማህበራቱም ለምርጫው ሰላማዊነት፣ ዴሞክራሲያዊነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት መምህር አካሉ አለማየሁ፤ የምርጫ ሂደት ለአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ስርዓትና ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ በምርጫው የፓርቲዎችን ፖሊሲና ስትራቴጂ በአግባቡ በመረዳት ህዝቡ በምርጫው ጠንካራ ተሳትፎ ማድረጉ አስፈላጊ ነው። በመሆኑም ግንዛቤ በመፍጠርና ለሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የሲቪክ ማህበራት የላቀ ሚና ይጠበቃል ያሉት ፕሬዚዳንቱ በዚሁ ልክ ለዘንድሮው ምርጫ መሳካት እየተዘጋጀን ነው ብለዋል። መምረጥ መሰልጠን መሆኑን ጠቁመው ለዚህም በተቀመጠው የጊዜ ሰለዳ መሰረት ካርድ መውሰድ እንደሚገባና ማህበሩም በዚህ ላይ ህብረተሰቡን በመቀስቀስ በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግ እየተሰራ ነው ብለዋል። የክልሉ ሴቶች ፌደሬሽን ስራ አስፈፃሚ እና የካፋ ዞን ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አስማረች ሀይሌ በበኩላቸው፣ ሴቶች በመመረጥ፣ በመምረጥና በመታዘብ መብታቸውን በተገቢው እንዲጠቀሙ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። የዘንድሮው ምርጫ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ መልኩ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ እንዲሆን የሴቶች ሚና የጎላ መሆኑን ጠቅሰው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ግንዛቤ የማስረጽ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ወጣቱ በታዛቢነትና በበጎ ፈቃድ አሰልጣኝነት ስለምርጫው ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በማስጨበጥ የተጠናከረ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንትና የካፋ ዞን አስተባባሪ ወጣት ፍሬው ደምሴ ገልጿል። በሁሉም የምርጫ ጣቢያ በታዛቢነት የሚሳተፉ ወጣቶች ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን ጠቁሞ ለምርጫው ስኬት ወጣቱ ሚናውን በተሻለ መልኩ እንዲወጣ ከምርጫ ቦርድና ከሌሎች ሲቪክ ማህበራት ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው ብሏል።
የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተሰራው ስራ ለውጥ ማምጣት ተችሏል
Feb 13, 2026 69
ነቀምቴ ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት ዓመታት በኢኮኖሚያዊ፣ በፖለቲካና በማህበራዊ መስክ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተሰራው ስራ ለውጥ ማምጣት መቻሉ ተገለጸ። በነቀምቴ ከተማ የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ ''በሴቶች ተሳትፎ የፀናችና የበለፀገች ኢትዮጵያ'' በሚል መሪ ሀሳብ የውይይት መድረክ ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት ሴቶች ክንፍ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ አሰለፈች ታደሰ እንደገለጹት፣ ባለፉት ዓመታት የሴቶች ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በሁሉም መስክ ውጤት እያሳየ ነው። ፓርቲው የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ፣ ወደ አመራር እንዲመጡ ለማገዝ፣ በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ እና የኑሮ ደረጃቸውን ለማሻሻል አበክሮ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። እስካሁን የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል የሴቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተው የሰላም እና የልማት እንቅስቃሴውን በማፋጠን ረገድ የሴቶች ተሳትፎ ይጠናከራል ብለዋል። በተለይ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ አሳታፊ፣ ፍትሃዊ እና ሰላማዊ እንዲሆን የድርሻቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው አስረድተዋል። በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ አያንቱ ይሻው በበኩላቸው፤ ሴቶች የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን በማጠናከር ረገድ ትልቅ ሚና አላቸው ብለዋል። በክልሉ በሁሉም ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሴቶች ተሳትፎን የማሳደግ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል። መጪው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን በተለይ የሴቶች አደረጃጀቶች ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ ነው ብለዋል። በዞኑ የሴቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የምስራቅ ወለጋ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ በጂ ሞሲሳ ናቸው። በግብርና፣ በንግድ እና በትምህርት የሴቶችን ተሳትፎ በማሳደግም ራሳቸውን ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲያደርሱ ይሰራል ብለዋል።
ፖለቲካ
ጨፌው በክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና ውስንነቶች ላይ በስፋት ይወያያል
Feb 13, 2026 8
አዳማ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የጨፌ ኦሮሚያ በክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና ውስንነቶች ላይ በስፋት እንደሚወያይ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን ገለፁ። የጨፌ ኦሮሚያ 6ኛ የስራ ዘመን 5ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ጉባኤ ነገ በአዳማ ገልመ ጨፌ መካሄድ ይጀምራል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን ጉባኤውን በማስመልከት መግለጫ በሰጡበት ወቅት ጨፌው በክልሉ ያለፉት ስድስት ወራት የመንግስት የስራ አፈጻጸም ዕቅድ ክንውን ላይ ውይይት ያደርጋል ብለዋል። በተለይ በግማሽ ዓመቱ የክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች የተገኙ ስኬቶችና ውስንነቶች ላይ ይወያያል ነው ያሉት። በተጨማሪም የጨፌው አባላትና ቋሚ ኮሚቴዎች በወረዳዎች፣ በከተሞችና በዞኖች ባደረጉት የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም በመስክ ምልከታ የተገኙ ሪፖርቶች ለጉባኤው ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸውም ጠቁመዋል። ጉባኤው የዳኞች ሹመትን ጨምሮ የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት በመወያየት ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክተዋል።
ሁለተኛው የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Feb 13, 2026 25
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/ 2018(ኢዜአ)፦ ሁለተኛው የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል። ጉባኤው የጣሊያን-አፍሪካ ግንኙነት በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብሮች ይበልጥ እንዲጠናከር የሚያደርግ ነው፡፡ ጉባኤው በአዲስ አበባ መካሔዱ ኢትዮጵያ አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር ያላትን አቅም እንደሚያሳይ ተገልጿል። ኢትዮጵያ 39ኛውን የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ እና የጣሊያን አፍሪካ ጉባዔን ለማስተናገድ ተዘጋጅታ እንግዶቿን እየተቀበለች ትገኛለች። የተለያዩ ሀገራት መሪዎችና የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ የተቋማት ኃላፊዎች አዲስ አበባ ይገኛሉ። የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው ነው።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አንድነትና ትብብር የምታበረክተው አስተዋጽኦ የአህጉሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለማፋጠን ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል
Feb 13, 2026 21
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አንድነትና ትብብር የምታበረክተው አስተዋጽኦ የአህጉሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርና ውህደት ለማፋጠን ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ሲሉ የኢኳቶሪያል ጊኒ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ማሪ-ክሩዝ ኢቩና አንዴሜ ገለጹ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካውያን የችግር ጊዜ ደራሽ፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ማስተሳሰሪያ ድልድይ መሆኑንም ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት 48ኛው የሥራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ትናንትና ከትናንት በስቲያ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ የሕብረቱ ዋና መስሪያ ቤት ሲካሄድ ቆይቶ ትናንት ተጠናቋል። 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔም "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ ነገና ከነገ በስትያ ይካሄዳል። የጉባኤው ተሳታፊ የኢኳቶሪያል ጊኒ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ማሪ-ክሩዝ ኢቩና አንዴሜ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ለደቡብ ደቡብ ትብብር መጎልበት ቁርጠኛ አቋም ያላት ሀገር ናት። ኢትዮጵያ በአህጉራዊ አንድነት ላይ ያላት ቁርጠኛ አቋም የደቡብ-ደቡብ ትብብርን በማጠናከር ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን ለማፋጠን ከፍተኛ አቅም እየሆነች እንደምትገኝም ገልጸዋል። ለአብነትም ከዓመታት በፊት የተከሰተው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥርጭትን ለመከላከል በተደረገው አህጉራዊ ጥረት ኢትዮጵያ የሕክምና ቁሳቁሶችን ለአፍሪካ ሀገራት በማዳረስ አስደናቂ አጋርነቷን በተግባር አሳይታለች ብለዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድም የወረርሽኝ መከላከያ መድኃኒትና ቁሳቁሶችን ለአፍሪካውያን በማዳረስ የችግር ጊዜ ደራሽ መሆኑን በተግባር ያስመሰከር ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የገነባው የተደራሽነት አድማስም የአፍሪካ ሀገራትን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር በማጠናከር አይነተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ኢትዮጵያ መሠረተ ልማቷን ለአፍሪካ እያጋራች መሆኑን ያሳያል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ በምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ውህደትም የመሪነት ሚና እየተወጣች ትገኛለች ነው ያሉት። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ መሆኗ በአህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ግንባር ቀደም ተዋናይነቷን በማጉላት የአፍሪካውያን አስተሳሳሪ ዋልታ እንድትሆን ማስቻሉን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤን በየዓመቱ በስኬት በማስተናገድ አህጉራዊ ትብብሮችን ለማጎልበት ትልቅ አቅም እየሆነች እንደምትገኝም ነው ጨምረው የገለጹት። ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አንድነትና ትብብር የምታበረክተው አስተዋጽኦ የአህጉሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርና ውህደት ለማፋጠን ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አብራርተዋል።
ምርጫው ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የምክር ቤት አባላት ሚና ወሳኝ ነው
Feb 13, 2026 43
አርባ ምንጭ ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የምክር ቤት አባላት ሚና ወሳኝ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አፈ- ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ አመለከቱ። የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአርባ ምንጭ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል። ዋና አፈ ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ በመክፈቻው መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ጠቅላላ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የምክር ቤት አባላት ሚና ሰፊ ነው ብለዋል። የለውጡ መንግስት የሀገራችንን ኋላ ቀር የፖለቲካ ልምምድ በመቀየር ሰው ተኮር የፖለቲካ ምህዳር በመትከል ሁለንተናዊ ልማት እያረጋገጠ ይገኛል ነው ያሉት። የጋራ ሀገርና የጋራ ሃሳብ ላይ የተመሠረተ ገዢ ትርክት በመገንባት የህዝቡን አንድነትና አብሮነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ምክር ቤቶች የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተምሳሌት እንደመሆናቸው መጠን የህዝቡ የልማት፣ የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱና የልማት ተጠቃሚነት ይበልጥ እንዲረጋገጥ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ አመልክተዋል። በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካዊ ዘርፎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ዋና አፈ ጉባኤው በንግግራቸው አንስተዋል። በክልሉ ያለውን ዕምቅ የግብርና አቅም ለመጠቀም የኩታ ገጠም እና የሜካናይዜሽን ልማትን ለማስፋፋት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ከልማዳዊ አሠራር በመውጣት ገበያን የሚያረጋጋ ምርት እንዲገኝ እያደረገ ስለመሆኑ ተናግረዋል። በመሠረተ ልማት፣ በትምህርትና በሌሎችም ዘርፎች ፍትሃዊ ተደራሽነትን በማረጋገጥ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ሰፊ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል። አቶ አለማየሁ፤ በክልሉ የተከሰተውን የማርበርግ ቫይረስ በህዝብና በአመራሩ የተቀናጀ ተግባር መቆጣጠር መቻሉንም አመልክተዋል። ክልሉን የሰላም፣ የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ በተደረጉ ጥረቶች በሁሉም አካባቢ ለውጥ ተመዝግቧል ብለዋል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው መደበኛ ጉባኤም የክልሉ መንግስት የ2018 ዓ.ም ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ማድመጥና ማጽደቅን ጨምሮ ልዩ ልዩ አዋጆችና ደንቦች እንዲሁም ሹመቶች እንደሚፀድቁም ይጠበቃል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገር የምታሸንፍበት እንዲሆን በቅንጅት እንሰራለን-የተፎካካሪ ፓርቲዎች
Feb 13, 2026 37
ባህርዳር፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገር የምታሸንፍበት እንዲሆን ቅንጅታቸውን የበለጠ እንደሚያጠናክሩ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ገለጹ። ''ለሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በጋራ እንቁም'' በሚል መሪ ሃሳብ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተፎካካሪ ፖርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መድረክ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ ተስፋሁን አለምነህ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና አሳታፊ እንዲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው። ምርጫው ሕግና አሰራርን ተከትሎ ሁሉም ፓርቲዎች በነፃነት የሚሳተፋበትና በሕዝብ ዘንድ አመኔታ ያተረፈ እንዲሆን ትብብርን የበለጠ ማጠናከር ይገባል ብለዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ስልጡን ፖለቲካን በማራመድ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። በምርጫ አሸናፊና ተሸናፊ መኖሩ ተፈጥሯዊ ቢሆንም በፋክክር ሂደቱ እኩል በመሳተፍ በምርጫው ሀገር እንድታሸንፍ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራሩን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምክር ቤቱ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊና አሳታፊ እንዲሆን ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። በምርጫ ሂደቱ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ መፍታት ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችና ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቀቀ
Feb 13, 2026 63
ታርጫ ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችን፣ ተጨማሪ በጀትና ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቀቀ። የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀን ውሎው የተለያዩ አዋጆችን፣ ተጨማሪ በጀትና ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቋል። በጉባኤውም ወደ ከተማ የተካለሉ ቀበሌዎችን የተመለከተ ሞሽን የቀረበ ሲሆን ይህም በየመዋቅሩ የሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለህዝቡ ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል። በዚህም መሰረት ከሸካና ቤንች ሸኮ ዞኖች 10 ቀበሌዎች ሙሉ በሙሉና በከፊል ወደ ቴፒና ሸኮ ዞኖች እንዲካለሉ በቀረበው የድጋፍ ሞሽን ላይ የምክር ቤቱ አባላት ውይይት አካሄደዋል። ሞሽኑን በተመለከተ ጥያቄና አስተያየቶች ቀርበው ምላሽ ከተሰጠበት በኋላ በአዋጅ ቁጥር 3/2018 ሞሽኑ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል። እንዲሁም ለኢኮኖሚው እገዛ ለማድረግ የሚያስችል የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ ደንብ ቀርቦ ውይይት ከተደረገ በኋላ በአዋጅ ቁጥር 49/2018 በሚል በሙሉ ድምፅ ሊፀድቅ ችሏል። በክልሉ ምክር ቤት ተጨማሪ የበጀት ረቂቅ ላይ ውይይት በማድረግ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የሚውል 657 ሚሊዮን 600 ሺህ ብር ተጨማሪ በጀትን ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል።ምክር ቤቱ በሁለተኛ ቀን ውሎውም ሌሎች አዋጆችን ማፅደቁም ተመልክቷል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ ለተለያዩ የሥራ ክፍሎች የቀረቡ እጩዎችን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል። በዚህም መሰረት፤- 1. አቶ ንጉሴ ወልደጊዮርጊስ፤ የክልሉ ሰው ሀብትና ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ 2. ረዳት ፕሮፌሰር ዘመድኩን ሰለሞን ፤የኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ ኃላፊ 3. አቶ መቱ አኮ፤ የክልሉ ቆላማና እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ቢሮ ኃላፊ 5. አቶ ታሪኩ አካሉ፤ የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም ሌሎች ሽግሽግ የተደረገባቸው ኃላፊዎች ዝርዝር ቀርቦ በምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል። ተሿሚዎችም በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል ።
ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የሲቪክ ማህበራት ዝግጅት ምን ይመስላል?
Feb 13, 2026 42
ቦንጋ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ ዘንድሮው በሚከናወነው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት እንዲሁም ለዜጎች የነቃ ተሳትፎ የላቀ ሚናቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚገኙ የሲቪክ ማህበራት ድርጅቶች ገለጹ። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሮ የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎቻቸውን እያስመዘገቡ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወጣው መርሃ ግብር እንደሚያመለክተው የመራጮች ምዝገባ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀምር ይሆናል። በዚህ የምርጫ ሂደት በተለይም የሲቪክ ማህበራት ግንዛቤ በመፍጠርና በታዛቢነት ጭምር በመሳተፍ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት መጎልበት የድርሻቸውን አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ይሆናል። ከዚህ አንፃር ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የሲቪክ ማህበራት ዝግጅት ምን ይመስላል? ሲል የኢዜአ ሪፖርተር በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚገኙ የሲቪክ ማህበራት ድርጅቶችን አነጋግሯል። የሲቪክ ማህበራቱም ለምርጫው ሰላማዊነት፣ ዴሞክራሲያዊነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት መምህር አካሉ አለማየሁ፤ የምርጫ ሂደት ለአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ስርዓትና ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ በምርጫው የፓርቲዎችን ፖሊሲና ስትራቴጂ በአግባቡ በመረዳት ህዝቡ በምርጫው ጠንካራ ተሳትፎ ማድረጉ አስፈላጊ ነው። በመሆኑም ግንዛቤ በመፍጠርና ለሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የሲቪክ ማህበራት የላቀ ሚና ይጠበቃል ያሉት ፕሬዚዳንቱ በዚሁ ልክ ለዘንድሮው ምርጫ መሳካት እየተዘጋጀን ነው ብለዋል። መምረጥ መሰልጠን መሆኑን ጠቁመው ለዚህም በተቀመጠው የጊዜ ሰለዳ መሰረት ካርድ መውሰድ እንደሚገባና ማህበሩም በዚህ ላይ ህብረተሰቡን በመቀስቀስ በምርጫው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግ እየተሰራ ነው ብለዋል። የክልሉ ሴቶች ፌደሬሽን ስራ አስፈፃሚ እና የካፋ ዞን ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አስማረች ሀይሌ በበኩላቸው፣ ሴቶች በመመረጥ፣ በመምረጥና በመታዘብ መብታቸውን በተገቢው እንዲጠቀሙ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። የዘንድሮው ምርጫ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ መልኩ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ እንዲሆን የሴቶች ሚና የጎላ መሆኑን ጠቅሰው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ግንዛቤ የማስረጽ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ወጣቱ በታዛቢነትና በበጎ ፈቃድ አሰልጣኝነት ስለምርጫው ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በማስጨበጥ የተጠናከረ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንትና የካፋ ዞን አስተባባሪ ወጣት ፍሬው ደምሴ ገልጿል። በሁሉም የምርጫ ጣቢያ በታዛቢነት የሚሳተፉ ወጣቶች ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን ጠቁሞ ለምርጫው ስኬት ወጣቱ ሚናውን በተሻለ መልኩ እንዲወጣ ከምርጫ ቦርድና ከሌሎች ሲቪክ ማህበራት ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው ብሏል።
የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተሰራው ስራ ለውጥ ማምጣት ተችሏል
Feb 13, 2026 69
ነቀምቴ ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት ዓመታት በኢኮኖሚያዊ፣ በፖለቲካና በማህበራዊ መስክ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተሰራው ስራ ለውጥ ማምጣት መቻሉ ተገለጸ። በነቀምቴ ከተማ የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ ''በሴቶች ተሳትፎ የፀናችና የበለፀገች ኢትዮጵያ'' በሚል መሪ ሀሳብ የውይይት መድረክ ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት ሴቶች ክንፍ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ አሰለፈች ታደሰ እንደገለጹት፣ ባለፉት ዓመታት የሴቶች ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በሁሉም መስክ ውጤት እያሳየ ነው። ፓርቲው የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ፣ ወደ አመራር እንዲመጡ ለማገዝ፣ በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ እና የኑሮ ደረጃቸውን ለማሻሻል አበክሮ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። እስካሁን የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል የሴቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተው የሰላም እና የልማት እንቅስቃሴውን በማፋጠን ረገድ የሴቶች ተሳትፎ ይጠናከራል ብለዋል። በተለይ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ አሳታፊ፣ ፍትሃዊ እና ሰላማዊ እንዲሆን የድርሻቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው አስረድተዋል። በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ አያንቱ ይሻው በበኩላቸው፤ ሴቶች የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን በማጠናከር ረገድ ትልቅ ሚና አላቸው ብለዋል። በክልሉ በሁሉም ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሴቶች ተሳትፎን የማሳደግ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል። መጪው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን በተለይ የሴቶች አደረጃጀቶች ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ ነው ብለዋል። በዞኑ የሴቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የምስራቅ ወለጋ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ በጂ ሞሲሳ ናቸው። በግብርና፣ በንግድ እና በትምህርት የሴቶችን ተሳትፎ በማሳደግም ራሳቸውን ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲያደርሱ ይሰራል ብለዋል።
ማህበራዊ
በጤና ዘርፍ የሚደረግ ኢንቨስትመንት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ ትልቅ መሠረት ይጥላል
Feb 13, 2026 10
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ በጤና ዘርፍ ላይ የሚደርግ ኢንቨስትመንት የሀገርን ምርታማነት ከማሳደግ ባለፈ ለዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ መሠረት መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ ገለጹ። ሚኒስትር ዴኤታው ይህንን የገለጹት “በኢትዮጵያ የወደፊት ዕድል ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፤ ከጤና ወጪ ወደ ጤና ኢንቨስትመንት” በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀው የዘላቂ ጤና ፋይናንስ የንቅናቄ ወርክሾፕ ላይ ነው። ዶክተር ደረጀ ድጉማ በዚሁ ወቅት፤ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ የሚመድበው በጀት ጤናማና አምራች ዜጋን በመፍጠር በኩል የላቀ ድርሻ አለው ብለዋል። እስካሁን ባለው ሂደትም በርካታ የጤና ተቋማት ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸውና ዘመናዊና ወሳኝ የሕክምና መሣሪያዎችን የማሟላት ሥራ፣ ብቁና በቂ የሰው ኃይል የማፍራት ተግባር መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ መንግሥት በቀጣይ የዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ ዘላቂ የፋይናንስ ሥርዓት መዘርጋትን እንደ ቀዳሚ ተግባር መያዙንም ጠቅሰዋል፡፡ የጤና ፋይናንስ ሥርዓቱ አስተማማኝ ወደ ሆኑ የሀገር በቀል የፋይናንስ ምንጮች መሸጋገር እንዳለበትም ነው የገለጹት፡፡ ይህንን ግብ ለማሳካትም በርካታ ተግባራት እንደሚከናወኑ ጠቁመው የፋይናንስ ምንጮችን በሀገር ውስጥ አቅም ማጠናከር፣ የጤና መድህን ሽፋንን በስፋት ማዳረስ እንዲሁም የግል ባለሀብቶችና አጋር አካላት በዘርፉ እንዲሳተፉ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ጤናማ ዜጋ ለሀገር እድገት ያለው ሚና የማይተካ መሆኑን በመጥቀስ፡፡ በመድረኩ የተገኙት በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት(WHO) የስትራቴጂክ ጤና ፖሊሲና ፕላን አስተባባሪ ዶክተር ቢጆይ ፒ. ናምቢያር፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ዘርፉን ለማዘመን እየከወናቸው ያሉ ተግባራት የሚደነቁ ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ የራሷን ዘላቂ የጤና ፋይናንስ ለማረጋገጥ የጀመረችው እንቅስቃሴ ወቅታዊና ስትራቴጂካዊ መሆኑንም ጨምረው ጠቁመዋል፡፡
የቤተሰብን የኢኮኖሚ አቅም በማሳደግ የመቀንጨር ችግርን ለማስወገድ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው
Feb 13, 2026 40
ሰቆጣ ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦የቤተሰብን የኢኮኖሚ አቅም በማሳደግና የአመጋገብ ሥርዓትን በማሻሻል የመቀንጨር ችግርን ለማስወገድ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። የሰቆጣ ቃልኪዳን ስምምነት (Sekota Declaration) መንግስት በ2030 ዓ.ም በሀገሪቱ የሚስተዋለውን የህፃናት የተመጣጠነ ምግብ እጥረትና የመቀንጨር ችግር ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት የገባው ቁርጠኝነት ነው። ነፍሰ-ጡር እናቶችና ከ5 ዓመት በታች ህፃናት ስርዓተ-ምግብን ማሻሻል፣ ምርታማነትን ማሳደግና አዕምሯዊና አካላዊ ዕድገት ቀውሶችን መከላከል የስምምነቱ ዋነኛ ግብ ነው። የመቀንጨርና የመቀጨጭ ችግር ከሚስተዋልባቸው አካባቢዎች አንዱ ዋግ ኽምራ ነው። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ሥርዓተ ምግብን የሚያሻሽሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። የሰቆጣ ቃል-ኪዳን ስምምነት እውን ከሚሆንባቸው ተግባራት አንዱ ሴቶችና እናቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡበት ሁኔታን መፍጠር ነው። ይህን ለማድረግ ከተወሰዱ እርምጃዎች አንዱ እናቶችን በእንስሳት ልማት ዘርፍ በማሰማራት የራሳቸውን ገቢ ከማመንጨት ባለፈ ለቤተሰቦቻቸው የተመጣጠነ ምግብ ማቅረብ የሚችሉበትን ሁኔታ ማመቻቸት ነው። በብሔረሰብ አስተዳደሩ በእንሰሳት እርባታ ዘርፍ የሥራ ዕድሉ ከተፈጠረላቸው እናቶች መካከል ሙሉ እሚያምረው አንዷ ናቸው። እርሳቸው እንደሚሉት፣ በተደረገላቸው የእንቁላል ጣይ ዶሮዎች ድጋፍ ከዕለት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ እያቀረቡ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል። ለራሳቸውና ለልጆቻቸው እንቁላልን ጨምሮ የተለያዩ የምግብ አይነቶችን በመመገብ ሥርዓተ-ምግባቸውን ለማሻሻልና ጤናቸውን በአግባቡ ለመጠበቅ እንዳስቻላቸውም ተናግረዋል። የጋዝጊብላ ወረዳ ነዋሪዋ አታላ ውቤ፤ ከዶሮ እርባታ ባለፈ በጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ በመሰማራት የቤተሰቦቻቸውን አመጋገብ ሥርዓት ማሻሻል እንደቻሉ ይገልጻሉ። በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት መምሪያ ኃላፊ ሲሳይ አያሌው እንደገለጹት፣ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የስርዓተ-ምግብን የሚያሻሽሉ ስራዎች እየተሰሩ ነው። የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮጀክትና ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የሕብረተሰቡ የአመጋገብ ሥርዓት እንዲሻሻል አጋዥ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት 20 ሺህ 800 የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶችን በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ለማሰማራት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አስታውሰው፣ ባለፉት ስድስት ወራት ከ12 ሺህ በላይ እናቶችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። እናቶች በዶሮ፣ በፍየልና በላም እርባታ ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ የልጆቻቸውንና የራሳቸውን የአመጋገብ ሥርዓት እንዲያሻሽሉና ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ዕድል መፈጠሩን ነው ያብራሩት፡፡
በአፍሪካ የጤና ዋስትናን ለማረጋገጥ ቀጣናዊ ትስስርንና ሁሉን አቀፍ ትብብርን ማጠናከር ወሳኝ ነው
Feb 13, 2026 37
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ የጤና ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ቀጣናዊ ትስስርንና ሁሉን አቀፍ ትብብርን ማጠናከር ወሳኝነት እንዳለው የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የአፍሪካ የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል ከአፍሪካ ልማት ባንክና ከአፍሪካ ህብረት የልማት ኤጀንሲ 'አውዳ-ኔፓድ' ጋር በመተባበር የአፍሪካ የጤና ዋስትና እና ሉዓላዊነት አጀንዳን ማሳካት በሚያስችሉ የፋይናንስ አማራጮች ላይ ያተኮረ ውይይት እየተካሄደ ነው። የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በአፍሪካ የጤና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ የክትትልና ስትራቴጂክ ፖሊሲዎች ላይ የተሻሉ ስራዎች ተሰርተዋል። አፍሪካ የጤና ዋስትና እና ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ አንስተው፤ የአፍሪካ ሲዲሲ የአህጉሪቱ የህብረተሰብ ጤና ላይ ፖለቲካዊ፣ ስልታዊ እና ቴክኒካዊ አመራር እንዲሰጥ በአፍሪካ ህብረት የተሰጠው ውሳኔ ይህን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። ተለዋዋጭ በሆነ ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ፣ ተደጋጋሚ ወረርሽኞች እየገጠሙ ባሉበት እና የውጭ ድጋፎች ባልተጠበቀ ሁኔታ እየቀነሱ መምጣት በአህጉሪቱ የዘርፉ ስራ ላይ ተጽዕኖ ከማሳደሩ በላይ በውጭ ድጋፍ ላይ ያለንን ጥገኝነት ያሳየ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመሆኑም አህጉራዊ አቅምን በማጠናከር ቀጣናዊ ትብብርን ማስፋት፣ የሀገር ውስጥ የቴክኒክ አቅምን ማጎልበት፣ ጠንካራ አስተዳደር መዘርጋት ለወደፊት አደጋዎች ዝግጁ ለመሆን ወሳኝ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአጭር ጊዜ የአደጋ ጊዜ የገንዘብ ምንጭን ወደ አስተማማኝ የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት መቀየር እንዲሁም በሀገር ውስጥ ማምረት የሚያስችል የመሠረተ ልማት አቅምን መገንባት እንደሚገባም ጠቁመዋል። ለዚህም የአፍሪካ ልማት ባንክ የመድኃኒትና የክትባት ምርትን ለመደገፍ የላቀ ሚና እንደሚኖረው ነው ሚኒስትሯ የገለጹት። የአፍሪካ ልማት ባንክ በፋይናንስ፣ የቀጣናዊ አጋሮች ቅንጅት፣ የግል ባለሀብቶች ተሳትፎ እንዲሁም የመንግሥታት ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል። ትልምን ወደ ተግባር መቀየር፣ ተቋማትን ማጠናከር፣ ቀጣናዊ አቅምን መገንባትና የሀገር ውስጥ ምርትን ማሳደግ ግድ የሚልበት ወቅት መሆኑን አንስተው፤ የፋይናንስ ውጤታማነትንና የአፍሪካን የጤና ሉዓላዊነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። የውይይት መድረኩ የአፍሪካን ጤና ዋስትና ለማረጋገጥና ዘላቂ የጤና ፋይናንስ ዘመን ለማራመድ ያለን የጋራ ቁርጠኝነት ነጸብራቅ ነው ሲሉም ገልጸዋል። በውይይቱ የአፍሪካ የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጄን ካሳይ፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኦልታ(ዶ/ር)፣ የአፍሪካ ህብረት የልማት ኤጀንሲ ዋና ስራ አስፈፃሚ ናርዶስ በቀለ፣ የአፍሪካ ሀገራት የጤናና ፋይናንስ ሚኒስትሮችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በጅማ ከተማ እየተገነባ ለሚገኘው የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት የ12 ኪሎ ሜትር የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ተከናወነ
Feb 13, 2026 40
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ከተማ እየተገነባ ለሚገኘው የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት 12 ኪሎ ሜትር የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ መከናወኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳመላከተው በጅማ ከተማ እየተገነባ ለሚገኘው የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት መጠነ ሰፊ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ዝርጋታ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ለፕሮጀክቱ ከጅማ አዲሱ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 12 ኪሎ ሜትር የሚረዝም 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር ዝርጋታ እና 300 የመካከለኛ መስመር ምሰሶ ተከላ ተከናውኗል ብሏል፡፡ በተመሳሳይ ሁለት ባለ 1ሺህ 250 ኪሎ ቮልት አምፒር፣ አንድ ባለ 630 ኪሎ ቮልት አምፒር ኮምፓክት ትራንስፎርመርና አንድ ባለ 200 ኪሎ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች መተከሉንም አገልግሎቱ ገልጿል፡፡ ከኃይል ማከፋፈያ ጀምሮ እስከ ፕሮጀክቱ ያለው የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ በሶስት ወራት በማጠናቀቅ ካለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ ለፕሮጀክቱ 5 ሜጋ ዋት ኃይል ማቅረብ ተችሏል ነው ያለው፡፡ የማሰራጫ መስመሩን ደረጃ የማስጠበቅና በኮንክሪት የመቀየር ስራውም 85 በመቶ መድረሱን አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡ አሁን ላይ ለስማርት ከተማው የቀረበው የኃይል መጠን 5 ሜጋ ዋት ቢሆንም በቀጣይ ለሚከናወኑ ሌሎች ትልልቅ ግንባታዎች ተጨማሪ 20 ሜጋ ዋት ኃይል ለማቅረብ እየተሠራ ይገኛል ነው ያለው በመግለጫው፡፡
ኢኮኖሚ
ለግብርና ልማት ሥራ ውጤታማነት በተሰጠው ትኩረት ተጠቃሚነታችን እያደገ ነው -አርሶ አደሮች
Feb 13, 2026 6
ሚዛን አማን ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦መንግሥት ለግብርና ልማት ሥራ ውጤታማነት በሰጠው ትኩረት ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ። የወረዳው አርሶ አደሮች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትና የሌማት ትሩፋት መርሀግብሮችን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ኢኒሼቲቮች የኢኮኖሚ አማራጮችን በማስፋት ገቢያቸውን እያሳደጉ ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል አርሶ አደር ጣሃ ሐቢብ እንዳሉት በቆሎ፣ ማሽላ፣ ቡና፣ ቁንዶ በርበሬ፣ እርድና ዝንጅብል በማልማት ኑሯቸውን እየመሩ ነው። ከግብርና ልማት ሥራቸውም ከዚህ ቀደም ከሚያገኙት የተሻለ ምርት በማምረት ገቢያቸውን እያሰደጉ መምጣታቸውን ተናግረዋል። ምርቶችን በጥራት አምርተን የልፋታችንን ያህል ውጤት እንድናገኝ በመንግስት በኩል የተሻሻለ ዝርያና የግብርና ግብአት አቅርቦት ድጋፍ ይደረግልናል ያሉት አርሶ አደር ጣሃ፣ የመንግስት እገዛና ክትትል ለስኬታማነታቸው አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የሌማት ትሩፋት መርሀግብር፣ የገጠር ኮሪደር እና መሰል የመንግሥት የልማት ኢኒሼቲቮች የኢኮኖሚ ምንጭ በመሆን የአርሶ አደሩን ሕይወት እያሻሻሉ መሆኑንም አክለዋል። የበጋ መስኖ ስንዴ፣ የሩዝና መሰል የሰብል ልማት ሥራዎች ተጠናክረው ከቀጠሉ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ ናቸው ያሉት ደግሞ አርሶ አደር አያሌው ኃይሉ ናቸው። በተለይ በቡና እና በቅመማ ቅመም ምርት የተሻለ ገቢ በማግኘት ለውጥ እንዲያመጡ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው ነው የገለጹት። የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን በምርምር ተቋማት በኩል መንግሥት እያቀረበ በመሆኑ በማሳቸው አላምደው ምርታማነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን የገለጹት ደግሞ አርሶ አደር ታምራት እረና ተናግረዋል። ሩዝን ጨምሮ በአካባቢው ያልተለመዱ ሰብሎችን በማልማት ውጤታማ መሆን እንደተቻለ ጠቅሰው መንግሥት ለግብርና ልማት የሰጠው ትኩረት ምርታማነታችንን የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል። የእርሻ ሥራቸው ውጤታማ እየሆነ በመምጣቱ ምርታቸውን ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉና ጥሪት እያፈሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሸካ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ አዕምሮ ደሳለኝ፤ በዞኑ የግብርና ኢኒሺየቲቭ ሥራዎች በአርሶ አደሮች ማሳ እንዲተገበሩ የተሰራው ሥራ ውጤት እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም በ10 አርሶ አደሮች ማሳ ከአራት ዓመት በፊት የተጀመረው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ዘንድሮ ከ2ሺህ 500 በሚበልጡ አርሶ አደሮች ማሳ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። በተመሳሳይ በ300 ሄክታር ማሳ ላይ የተጀመረው የሩዝ ልማት ዘንድሮ ወደ 3ሺህ 200 ሄክታር ማደጉን ገልጸው፣ በሌማት ትሩፋትም እየመጣ ያለው ውጤት እንዲጠናከር በመምሪያው በኩል ድጋፍና ክትትሉ መጠናከሩን ጠቁመዋል።
የአገልግሎት አሰጣጥ መዘመንና የመሰረተ ልማት መሟላት ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እያደረጋት ነው
Feb 13, 2026 16
ኮምቦልቻ ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦የአገልግሎት አሰጣጥ መዘመንና የመሰረተ ልማት መሟላት ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እያደረጋት መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) ገለጹ። በኮሚሽኑ የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈጻሚዎች የጋራ የምክክር መድረክ በኮምቦልቻ እየተካሄደ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር)፤የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን በማሟላትና አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን መሳብ ተችሏል ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት በዘርፉ ላይ ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን ጠቅሰው፤ ከ2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ካፒታል ያላቸው የውጭ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰሳቸውን ተናግረዋል። ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ20 በመቶ ጭማሬ አለው ብለዋል። አክለውም በፌዴራል ደረጃ ለ245 የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል። ባለፉት ስድስት ወራት የቻይና፣ የህንድ፣ የአሜሪካ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና የሌሎች አገራት ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት ፍቃድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። የአገልግሎት አሰጣጡ መዘመንና የመሰረተ ልማት መሟላት ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እያደረጋት መሆኑንም ኮሚሽነሩ አመልክተዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የክልሉን ሰላም በማጽናት የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ ናቸው ብለዋል። ባለፉት ስድስት ወራት በክልሉ ከፍተኛ ሃብት ላስመዘገቡ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ጠቁመው፣ የመሰረት ልማቱንና አገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል ወደ ሥራ እንዲገቡም እየተደረገ ነው ብለዋል።
የግብርና ሜካናይዜሽን አጠቃቀም ማደግ በሰብል ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ውጤት አስገኝቷል
Feb 13, 2026 65
ባህር ዳር ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብርና ሜካናይዜሽን አጠቃቀም ማደግ በሰብል ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተጻፈው የመደመር መንግስት መጽሐፍ እንደተመላከተው፣ የእርሻ ሜካናይዜሽን ሽግግር የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው። በመሆኑም ዘመናዊ የእርሻ ማሽነሪዎችን ወደ እርሻ ማምጣትና አርሶ አደሩን ማስታጠቅ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ በመሆኑ አርሶ አደሩ ትራክተሮችን በቁጠባና በብድር የሚያገኝበት መንገድ እየተተገበረ መሆኑን መጽሐፉ ያብራራል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አጀበ ስንሻው፤ መንግስት በዘንድሮው የበጀት ዓመት በግብርናው ዘርፍ ለማስመዝገብ የያዘው እቅድ እንዲሳካ ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችን መጠቀም ወሳኝ መሆኑን ያነሳሉ። የግብርና ሜካናይዜሽን የሰብል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና ግብርናውን ትራንስፎርም ለማድረግ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። በክልሉ በበጀት ዓመቱ አንድ ሺህ 400 የእርሻ ትራክተሮችንና የሰብል ማጨጃና መውቂያ ኮምባይነሮችን ለአርሶ አደሩ፣ ለህብረት ስራ ማህበራትና ለባለሃብቶች ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እስካሁን 536 ያህሉ መሰራጨቱን ገልጸዋል። እንዲሁም 878 አነስተኛ የሰብል ማጨጃ መውቂያና የበቆሎ መፈልፈያ ማሽኖችና 5 ሺህ 48 የውሃ መሳቢያ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል። በክልሉ የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂ እየተስፋፋ መምጣት የሰብል ምርታማነትን በማሳደግ በኩል ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን አብራርተዋል። በክልሉ በ2017/18 የምርት ዘመን በትራክተር አንድ ሚሊዮን 35 ሺህ ሄክታር መሬት ማረስ የተቻለ ሲሆን በዋና ዋና ሰብሎች አማካኝ የሰብል ምርታማነትን በሄክታር ከ37 ነጥብ 5 ኩንታል ወደ 41 ነጥብ 4 ኩንታል ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። ለምርታማነቱ መጨመር በዋናነት የተጠቀሰው የግብርና ሜካናይዜሽን መስፋፋት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በግለሰብ አርሶ አደሮች ዘንድ የውሃ ፓምፖች አጠቃቀም ማደጉና አርሶ አደሩ በክላስተር በመደራጀት ቴክኖሎጂን መጠቀሙ እንዲሁም ሌሎች የግብርና ዘርፉን ውጤታማ የሚያደርጉ ስራዎች ለውጤቱ መገኘት ድርሻ አላቸው ብለዋል። አርሶ አደሩ በትራክተር መሬቱን የማረስ ልምድና ፍላጎቱ በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰው፤ መሬትን በትራክተር ማረስ የአፈር ለምነት እንዲጨምርና ውሃን በውስጡ አስርጎ እንዲይዝ ያደርጋል ነው ያሉት። በእንጅባራ ከተማ የሚገኘው የአድማስ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ መሰረት ወርቄ፤ የአርሶ አደሩ የሜካናይዜሽን የእርሻ ልምምድና ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል። በተያዘው ዓመት ዩኒየኑ 21 ትራክተሮች ግዥ በመፈፀም ለአባል አርሶ አደሮች በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም አርሶ አደሩ የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂን በአግባቡ ተጠቅሞ ትርፍ ምርት በማምረት ለገበያ እያቀረበና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው ብለዋል።
በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ንግድና ኢንቨስትመንትን እያነቃቁ ነው
Feb 13, 2026 78
ሳውላ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦በሳውላ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የከተማዋን ንግድና ኢንቨስትመንት እያነቃቁ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ንጉሴ መኮንን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከተማዋ የሴክተር መስሪያ ቤቶች ማዕከል በመሆኗ አካባቢዋን ምቹና ሳቢ የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል። በተያዘው ዓመት የሁለት ባለ ኮከብ ሆቴሎች ግንባታን ጨምሮ ሌሎች የንግድ ተቋማት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው የልማት ስራ መጀመራቸውንም አስታውቀዋል። ይህም የከተማዋን የገቢ አቅም ለማሳደግ እያስቻለ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ብቻ ከመደበኛ ገቢ 152 ሚሊዮን ብር መገኘቱን አመልክተዋል። በዘንድሮው ዓመት የተገኘው ገቢ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘው 56 ሚሊዮን ብር ጋር ሲነፃፀርም ከፍተኛ ልዩነት እንደሚያሳይም ነው የተናገሩት። በከተማዋ በአሁኑ ወቅት ከ5 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሆን የመንገድ ከፈታን ጨምሮ የሁለት ድልድይ ግንባታን በማከናወን ነዋሪው ለረዥም ጊዜያት ሲያነሳቸው ለነበሩ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ተችሏል ነው ያሉት ። በአሁኑ ወቅት በከተማዋ የሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ የተጀመረ ሲሆን በአንደኛው ዙር የተካሔደው የአንድ ኪሎሜትር የኮሪደር ልማት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉንም ነው የጠቀሱት። በከተማዋ የቀበሌ 04 ነዋሪ አቶ ስዩም ሱምሳ፤ በሚኖሩበት አካባቢ የመሻገሪያ ድልድይ ባለመኖሩ ረጅም የእግር ጉዞ በማድረግ ከፍተኛ እንግልት ይደርስባቸው እንደነበር ይናገራሉ። በአሁኑ ወቅት በከተማዋ ከተካሄደው የመሰረተ ልማት ግንባታ ውስጥ የመሻገሪያ ድልድይ እንዲኖር በመደረጉ ችግሩ መፈታቱን እና እፎይታ ማግኘታቸውን ነው የሚናገሩት። በአካባቢው የመንገድ ከፈታ እና የድልድይ ግንባታ መካሔዱ ወደ ተለያዩ ቦታዎች የምናደርገውን የረጅም ርቀትና አድካሚ ጉዞ አስቀርቶልናል ያሉት ደግሞ የአካባቢው ነዋሪ የሆኑት ቄስ ዘርይሁን ገብረኪዳን ናቸው። ወጣት ተክሌ ካሻ በበኩሉ በከተማዋ እየተከናወኑ ባሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ከሌሎች ወጣቶች ጋር በመደራጀት የስራ እድል ተጠቃሚ መሆኑን ነው የተናገረው።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የሠመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጉላላትን አስቀርቷል
Feb 13, 2026 63
ሠመራ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የሠመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉዳያቸውን በፍጥነት በመጨረስ መጉላላትን እንዳስቀረላቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናገሩ። የሰመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፣ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሸነር መኩሪያ ኀይሌ(ዶ/ር) እና የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በተገኙበት ህዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም ተመርቆ ስራ መጀመሩ ይታወሳል። ማእከሉ ለደንበኞች የተቀላጠፈ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ በማሳደጉ ተግባሩን ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች የማስፋት ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ማዕከሉ የዘረጋው የተቀላጠፈ አገልግሎት ጊዜና ገንዘባቸውን ከብክነት በማዳን እንግልትን እንዳስቀረላቸው የሰመራ ሎጊያ ነዋሪዎች ለኢዜአ ገልጸዋል። የአገልግሎት አሰጣጡን አስመልክቶ ሀሳባቸውን ከሰጡ ተገልጋዮች መካከል የሠመራ ከተማ ነዋሪው አቶ ሀቢብ መሐመድ፤ የሰመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ መስሪያ ቤቶችን በአንድ ላይ በማግኘት በአጭር ጊዜ ጉዳያቸውን ለመጨረስ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። ይህም ከመጉላላትና ከተጨማሪ ወጪዎች እንደታደጋቸውና ጊዜያቸውን በተገቢው እንዲጠቀሙ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል። ማዕከሉ የተለያዩ ተቋማትን አገልግሎቶች አቀናጅቶ መያዙ ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ ያሲን ሁሴን ናቸው። ይህም በተለይም ከንግድ ፈቃድ ዕድሳት ጋር ተያይዞ ይወስድ የነበረውን ረጅም ጊዜ ማስቀረት የቻለ መሆኑን ተናግረዋል። የሠመራ ሎጊያ ነዋሪው አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ በአንድ ቦታ በመሆኑና በቴክኖሎጂ በመታገዝ አገልግሎት ማግኘት ችያለሁ ብለዋል። የሠመራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ከሊል አሊ፤ ማዕከሉ በአምስት ተቋማትና በ13 አገልግሎት ዘርፎች አገልግሎት መጀመሩን አስታውሰው አሁን አገልግሎቱ ወደ 29 ዘርፎች ማደጉን ተናግረዋል። በዚህም በሶስት ወራት ውሰጥ 7ሺህ 800 ለሚሆኑ ባለጉዳዮች አገልግሎት መሰጠቱን ገልፀዋል። ይህም የማህበረሰቡን እንግልትን እንዲሁም ብልሹ አሰራሮችን ለመቅረፍ በማገዙ ስራውን ይበልጥ በማስፋት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
አፍሪካ በራሷ አቅም የቴክኖሎጂ ስራዎችን በማከናወን ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ የጋራ ጥረትና ርብርብ ማድረግ ይገባል
Feb 12, 2026 129
አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በራሷ አቅም የቴክኖሎጂ ስራዎችን በማከናወን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ የጋራ ጥረትና ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና ገለፁ። ኮሚሽነሩ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ሳይንስ ለአፍሪካ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ መሆኑን ገልፀዋል። ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በአፍሪካ የትምህርት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ስትራቴጂ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በዚህም የትምህርት ተደራሽነት፣ የመምህራን ልማት፣ ጥናትና ምርምሮችን ወደ ንግድ መለወጥ እንዲሁም ከዲጂታልና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ጋር የተጣጣመ ክህሎት ማበልጸግ ላይ እንደሚተኮር ገልፀዋል። አፍሪካ ከተፈጥሮ ሀብት በተጨማሪ ትልቁ ሀብቷ የሰው ኃይል መሆኑን አንስተው፤ ትምህርት ክህሎትን በማሳደግ የአፍሪካን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በ2034 ሁሉም በአፍሪካ ያሉ ህፃናት መሰረታዊ ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ፣ ብቁ መምህራን ማፍራት የሚያስችል ስልጠና መስጠትና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የጥናትና ምርምር እንዲሁም ችግር ፈቺ ስራዎች የሚያበረክቱ መሆን አለባቸው ብለዋል። የትምህርት ተደራሽነትን እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ስልጠናን ማስፋት ለአረንጓዴና ዲጂታል ኢኮኖሚ አስተዋፅኦ ያለው ዜጋ መፍጠርና የመምህራን ልማት እንዲሁም የመሰረተልማት ውስንነትን ለመፍታት ሰው ሰራሽ አስተውሎትና ቴክኖሎጂ መጠቀም እንደሚገባ ገልፀዋል። ዘላቂ የፋይናንስ አቅርቦት ማቅረብ የሚያስችል ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው፤ አህጉር አቀፍ የስትሪንግ ኮሚቴ በማቋቋም እንደሚሰራ ተናግረዋል። አፍሪካ ምርምርን ወደ ምርት መቀየር እንዲሁም ፈጠራን ወደ ስራ እድል መፍጠር የሚያስችል ተግባር ማከናወን እንደሚገባ ጠቁመው ለዚህም የሁሉም አጋር አካላት ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል። አህጉሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን ካልቻለች በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ተወዳዳሪነት ማረጋገጥ እንደማትችልም ነው የገለጹት። አህጉሪቱ ለሚቀጥሉት አስር ዓመታት የምትመራበትን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስትራቴጂ ይፋ ተደርጓል። አፍሪካ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ሳይሆን ፈጣሪ መሆን አለባት ያሉት ኮሚሽነሩ፣ ህብረቱ የራሱን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስታንዳርድና መመሪያ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል። ይህ መመሪያ ቴክኖሎጂው ከአፍሪካ ባህልና እሴት ጋር ተስማምቶ እንዲለማ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል። በአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰሩ ምርምሮች ወደ ምርትና አገልግሎት ተቀይረው ለህብረተሰብ ችግር መፍትሄ እንዲሆኑ ከግል ዘርፉ ጋር ጠንካራ ትስስር እንደሚፈጠር ተናግረዋል።
በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች ውጤት እያመጡ ነው -አቶ አወሉ አብዲ
Feb 12, 2026 92
ሞጆ ፤የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ ገለፁ። የሞጆ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ወደስራ ገብቷል። የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ ማዕከሉን መርቀው አገልግሎት ሲያስጀምሩ አንደገለጹት በክልሉ የመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ ለዲጂታላይዜሽን ትኩረት ተሰጥቷል። ለዚህም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫን ተደራሽ ለማድረግ በመጀመሪያ ምዕራፍ በአዳማ፣ ሻሸመኔ፣ ሸገር፣ ቢሾፍቱና ጂማ ከተሞች ወደስራ ማስገባቱን አስታውሰዋል። ተግባሩን በማጠናከርም ወደ 26 ከተሞች እየተስፋፋ መሆኑን ጠቅሰው የዛሬ የሞጆ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ መጀመር የዚሁ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የከተማ አስተዳደሩ የህንፃ ግንባታውን በፍጥነት በማጠናቀቅ ከወረቀት ንኪኪ ነፃ የሆነ ዲጂታል አገልግሎት ማስጀመር መቻሉን ገልጸዋል። የማዕከሉ ሙያተኞችም ህብረተሰቡን በስነ-ምግባርና በታማኝነት በማገልገል የአገልግሎት አሰጣጥ ዕርካታን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል ። በሶስተኛ ምዕራፍ በክልሉ 60 ከተሞች የመሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ለማስጀመር ግብ መቀመጡን አንስተዋል። በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ የኮሪደር ልማት፣ የገቢ አሰባሰብና የልማት ስራዎች ማጠናከር ላይ በትኩርት ይሰራል ብለዋል። የሞጆ ከተማ ከንቲባ አቶ ገዛሊ ሀሹ በበኩላቸው በከተማዋ መልካም አስተዳደርን በማስፈን ቀልጣፋ የህዝብ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እይተደረገ ብለዋል። ለዚህም በተለያዩ ተቋማት ሲሰጥ የነበረውን የመንግስት አገልግሎቶች በመሶብ የአንድ አገልግሎት ማእከል መስጫ በማሰባሰብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር መዘርጋቱ አንስተዋል። ''ማዕከሉ የህዝቡ ዕንግልት ከማስቀረት ባለፈ የአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎችን የሚቀርፍ ነው'' ያሉት ከንቲባው ጥራት ያለው ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ እንዲቻል የማዕከሉ ሙያተኞችን በስነ ምግባር፣ በትምህርት ዝግጅት መመደቡን ተናግረዋል ። ማእከሉ የ23 መስሪያ ቤቶች፣ በ12 መስኮቶች 106 አገልግሎቶች እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። የማእከሉን ስራ መጀመር አስመልክተው አስተያየት ከሰጡ የሞጆ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ አስቴር ቢራ እንደገለፁት ማእከሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ማዘመኑ እንግልትን የሚያስቀር ነው። ይህም ጊዜና ገንዘባቸውን ከመቆጠብ ባለፈ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን በአንድ ቦታ አገልግሎት ማግኘት እንደሚያስችላቸው ጠቁመዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ሙሉ ቸርነት በበኩላቸው መስተዳድሩ የህዝቡን ቅሬታ ለመፍታት መሶብ የአንድ ማእክል አገልግሎትን ስራ ማስጀመሩ የሚበረታታ ነው ብለዋል። ባንኮች ጨምሮ በአገልግሎት መስጫ ማዕከሉ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸው ከመስሪያ ቤት ወደ መስሪያ ቤት የነበረውን ምልልስ በማሳጠር ፈጣን አገልግሎት እንድያገኙ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ወስደዋል-ቢሮው
Feb 12, 2026 83
ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች በነጻነት ለመንቀሳቀስ የሚያስችላቸው ነው። መታወቂያው የዜጎችን ትክክለኛ ማንነት ለመለየትና የወንጀል ድርጊቶችን በመከላከል ለማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ዋስትና መረጋገጥ ጠቀሜታ እንዳለውም አንስተዋል። በክልሉም ነዋሪዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። እስካሁንም መታወቂያውን ለማግኘት ከተመዘገቡት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሚሆኑት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መታወቂያውን ለመውሰድ የተመዘገቡ ነዋሪዎች ቁጥር እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ "በበጀት ዓመቱ ለ6 ሚሊዮን ዜጎችን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ ነው" ብለዋል። የፋይዳ መታወቂያ አይነስውራን አገልግሎት ለማግኘት ይደርስብን የነበረውን እንግልት በመቀየር ትልቅ ለውጥ አምጥቷል ያለው ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ ተማሪ መሸሻ ማንዳዶ ነው። መታወቂያው በተለይ እንደእሱ አይነስውራን ለሆኑ ዜጎች ተደራሽ በመደረጉ እንግልቶችን ከማስቀረት ባለፈ በነፃነት ለመንቀሳቀስ አስችሎናል ነው ያለው። አቶ መሳይ ሳሙኤል የተባሉ ሌላው አስተያየት ሰጪ በበኩላቸው "የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በንግድ ሥራችን ላይ ሊደረስ የሚችል መጭበርበርን እየታደገ ነው" ብለዋል። መታወቂያው የዜጎችን ትክክለኛ መረጃ በተሻለ መንገድ እንዲያዝ በማድረጉ ወንጀልና ወንጀለኞችን በቀላሉ ለመከላከል የጎላ አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ቴዎድሮስ ዘካሪያስ በበኩላቸው፤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸው በንግድም ሆነ በሌሎች ተግባራት ደሕንነቱ የተጠበቀ እንቅስቃሴ ለማድረግ እንደረዳቸው ተናግረዋል።
ስፖርት
በስፔን ጥሎ ማለፍ የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ ጨዋታ አትሌቲኮ ማድሪድ ባርሴሎናን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ
Feb 13, 2026 77
አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፦ በስፔን ጥሎ ማለፍ (ኮፓ ዴል ሬይ) የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ ጨዋታ አትሌቲኮ ማድሪድ ባርሴሎናን 4 ለ 0 ረቷል። ማምሻውን በዋንዳ ሜትሮፖሊታኖ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አንቶዋን ግሪዝማን፣ ጁሊያን አልቫሬዝ፣ አዲስ ፈራሚው አዴሞላ ሉክማን እና የባርሴሎናው ግብ ጠባቂ ኤሪክ ጋርሺያ በራሱ ላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በመጀመሪያው አጋማሽ ፍጹም የጨዋታ ብልጫ የወሰደው አትሌቲኮ ማድሪድ በ45 ደቂቃ አራት ግቦችን አስቆጥሯል። የባርሴሎናው ተከላካይ ኤሪክ ጋርሺያ በ86ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ባርሴሎና በሁለተኛው አጋማሽ ወደ ጨዋታው ለመመለስ ቢሞክርም አትሌቲኮ ማድሪድ ውጤቱን ማስጠበቅ ችሏል። አትሌቲኮ ማድሪድ ወደ ፍጻሜ የማለፍ እድሉን አስፍቷል። አስደንጋጭ ሽንፈት ያስተናገደው ባርሴሎና ውጤቱን የመቀልበስ ከባድ ፈተና በመልሱ ጨዋታ ይጠብቀዋል። የመልሱ ጨዋታ የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በካምፕ ኑ ስታዲየም ይደረጋል። ትናንት በተደረገው ሌላኛው የስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ ጨዋታ ሪያል ሶሳዬዳድ ከሜዳው ውጪ አትሌቲኮ ቢልባኦን 1 ለ 0 አሸንፏል። የመልሱ ጨዋታ የካቲት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ባርሴሎና የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ነው።
አርሰናል ከብሬንትፎርድ ጋር አቻ ተለያየ
Feb 12, 2026 88
አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ብሬንትፎርድ እና አርሰናል ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ አጠናቋል። ማምሻውን በጂቴክ ኮምዩኒቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኖኒ ማኑዌኬ በ61ኛው ደቂቃ በግሩም ሁኔታ በግንባሩ በመግጨት ያስቆጠረው ግብ መድፈኞቹን መሪ አድርጓል። በ71ኛው ደቂቃ ከረጅም እጅ ውርወራ የተገኘውን ኳስ ኪን ሉዊስ-ፖተር በግንባሩ ገጭቶ ከመረብ ላይ ባሳረፋት ጎል ብሬንትፎርድ አቻ ሆኗል። ብሬንትፎርድ በሊጉ ከእጅ ውርወራ አራተኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል። በጨዋታው አርሰናል ከብሬንትፎርድ ጠንካራ ፉክክር ገጥሞታል። ሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ የተደረገበት ሲሆን ሁለቱም ቡድኖች ጨዋታውን የማሸነፍ እድላቸውን መጠቀም አልቻሉም። በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ነጥብ የጣለው የሊጉ መሪ አርሰናል ነጥቡን ወደ 57 ከፍ አድርጓል። ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ከስድስት ወደ አራት ዝቅ ብሏል። ብሬንትፎርድ በ40 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች አልተሸነፈም።
ሊቨርፑል ሰንደርላንድን አሸነፈ
Feb 12, 2026 105
አዲስ አበባ ፤ የካቲት 4/2018 (ኢዜአ)፡- በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት ጨዋታ ሊቨርፑል ሰንደርላንድን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በስታዲየም ኦፍ ላይት በተካሄደው ጨዋታ አምበሉ ቨርጅል ቫን ዳይክ በ61ኛው ደቂቃ ከማዕዘን ምት የተሻገረውን ኳስ በግንባሩ በመግጨት ያስቆጠራት ግብ ቀያዮቹን አሸናፊ አድርጋለች። በጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ሰንደርላንድ፣ ሊቨርፑል በሁለተኛው አጋማሽ ብልጫ ወስደው ተጫውተዋል። ጃፓናዊው የሊቨርፑል የተከላካይ አማካይ ዋታሩ ኤንዶ ባጋጠመው ከፍተኛ ጉዳት ምክንያት በ69ኛው ደቂቃ በጆ ጎሜዝ ተቀይሮ ወጥቷል። የሊቨርፑል የተከላካይ ክፍል ጉዳት ቀውስ ተባብሶ ቀጥሏል። በሊጉ 12ኛ ድሉን ያስመዘገበው የወቅቱ የዋንጫ ባለቤት ሊቨርፑል በ42 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ስምንተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሰንደርላንድ በ36 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሊጉ በሜዳው ሽንፈት ሳያስተናግድ የቆየው ብቸኛው ክለብ ሰንደርላንድ ለመጀመሪያ ጊዜ በስታዲየም ኦፍ ላይት ተሸንፏል። በሌላኛው ጨዋታ በርንሌይ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 2 አሸንፏል።
ማንችስተር ሲቲ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል
Feb 12, 2026 101
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 3 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በኢትሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አንቶዋን ሴሜንዮ፣ ኒኮ ኦራይሊ እና አርሊንግ ሃላንድ የማሸነፊያ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ማንችስተር ሲቲ በተጋጣሚው ላይ ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል። ውጤቱን ተከትሎ በውድድር ዓመቱ 16ኛ ድሉን ያስመዘገበው ማንችስተር ሲቲ በ53 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት በጊዜያዊነት ወደ ሶስት ዝቅ አድርጓል። ውሃ ሰማያዊዎቹ በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝተዋል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 12ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ፉልሃም በ34 ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።በሊጉ ተከታታይ ሽንፈቱንም አስተናግዷል። የማንችስተር ሲቲው አጥቂ አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 22 ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት መሪነቱን አጠናክሯል። በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው መርሐ-ግብር አስቶንቪላ ብራይተንን በታይሮን ሚንግስ ጎል 1 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎ ቪላ ነጥቡን ወደ 50 ከፍ በማድረግ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። ብራይተን በ31 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ኖቲንግሃም ፎረስት እና ዎልቭስ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ በውኃ ዘላቂነትና ተደራሽነት ረገድ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች ነው
Feb 12, 2026 108
አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በውኃ ዘላቂነትና ተደራሽነት ረገድ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች መሆኗን የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ ምክር ቤት ሴክሬታሪያት ገለጸ። የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ ምክር ቤት ሴክሬተሪያት ኃላፊ ዊሊያም ካሪው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት እያሳየ ያለው የአመራር ሚና ለአፍሪካ ኅብረት እጅግ መሰረታዊ መሆኑን ጠቁመዋል። የኅብረቱ አባል ሀገራት በማንኛውም አባላት ዘንድ የተዘረጉ መልካም ተሞክሮዎችንና ፖሊሲዎችን በአርዓያነት መጠቀም እንዳለባቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት ለዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ተደራሽነት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ፖሊሲዎችንና አሠራሮችን መዘርጋቱን ገልጸው፤ ይህም ለሌሎች የአፍሪካ ኅብረት አባል ሀገራት መልካም ተሞክሮ መሆኑን አስታውቀዋል። በተወሰዱ የፖሊሲ ለውጦችና ቆራጥ የአመራር ሰጭነት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችውን ስኬትም አድንቀዋል። ይህ ትልቅ ቁጥር መሆኑን ጠቁመው፤ የአመራርና ትክክለኛ ፖሊሲዎች ውጤት መሆኑን አስረድተዋል።
የተፋስስ ልማት ሥራ የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርታማነትን በማሳደጉ አጠናክረን ቀጥለናል
Feb 12, 2026 82
ወልቂጤ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፡-የተፋሰስ ልማት ሥራ የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርታማነትን እያሳደገ በመሆኑ ዘንድሮም አጠናክረው መቀጠላቸውን የጉራጌ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ፡፡ አርሶ አደሮቹ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች የአፈር ለምነትን በመጠበቅና የተጎዱ መሬቶች እንዲያገግሙ በማድረግ ምርታማነትን እያሳደገ በመሆኑ ዘንድሮም ልማቱን ማጠናከራቸውን ገልጸዋል። በጉራጌ ዞን የእኖር ኤነር መገር ወረዳ አርሶአደር በደዊ ታቅንዳ በተፋሰስ ልማት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ መጀመሩ በጎርፍ ተጠርጎ ይወሰድ የነበረ ለም አፈር ጥቅም ላይ ለማዋል አስችሏል ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ሥራዎች የተራቆቱ መሬቶች ማገገማቸው እና የደረቁ ምንጮች ዳግም መፍለቃቸው የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውን ተናግረዋል። በዚህም በዘንድሮ የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ሥራ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን ጠረጴዛማ የእርከን ልማት ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላኛው የእዣ ወረዳ አርሶ አደር ወይዘሮ ሙርጋት ታቅንዳ በበኩላቸው ባለፉት ተከታታይ ዓመታት የተከናወነው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ መሬታቸውን ከመሸርሸር መታደጉን ገልጸዋል። የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ የመሬት ለምነትን በመመለስ ምርታማነትን እያሳደገ በመሆኑ በዘመቻው በንቃት እየተሳተፉ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ የተጎዱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙና ምርታማነታቸው እንዲጨምር ማድረጉን የተናገሩት ሌላኛው የእኖር ወረዳ አርሶ አደር መህዲ ደሊል ናቸው። የተፋሰስ ልማት ሥራው እየተመናመኑ የነበሩ የደንና የውኃ ሀብቶች እንዲመለሱ ማስቻሉንም ገልፀዋል ። የለሙ አካባቢዎችን ከሰውና ከእንስሳት ንኪኪ በመጠበቅ ለመኖ ልማትና ለንብ ማነብ ሥራ በማዋል ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እያስቻሉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በበኩላቸው እንዳሉት ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራዎች ውጤት ተመዝግበዋል። በተለይም ተዳፋታማ በሆኑ አካባቢዎች ጠረጴዛማ እርከን በመስራት ከምርት ውጭ የነበሩ መሬቶች አገግመው በተለያዩ ሰብሎች እንዲለማ ከመደረጉ ባለፈ ለንብ ማነብ ሥራ እየዋሉ መሆኑን ገልጸዋል። የደረቁ ምንጮችና በጎርፍ በመሸርሸር የተጎዱ መሬቶች ማገገማቸው የግብርና ምርትና ምርታማነትን እያሳደገው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶች አርሶ አደሩን ተጠቃሚ በማድረጋቸው በዘንድሮ ተፋሰስ ልማት የወጣቶችና የሴቶች ተሳትፎ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ገልጸዋል። በዘንድሮ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት ሥራ በዞኑ በ23 ሺህ ተፋሰሶች ላይ 88 ሺህ 581 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በአፍሪካ የውሃ ዋስትናን ለማረጋገጥ አርዓያነት ያለው ተግባር ነው
Feb 9, 2026 186
አዲስ አበባ፤ የካቲት 2/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራና ተፋሰስ ልማት ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በአፍሪካ የውሃ ዋስትናን ለማረጋገጥ አርዓያነት ያለው ተግባር ነው ሲሉ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በአፍሪካ ሕብረት የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ባህል ምክር ቤት "የአጀንዳ 2063 ግቦች ለማሳካት ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ" የሚለውን የ39ኛው የሕብረቱን መሪ ቃል በተመለከተ የሲቪል ማህበረሰብ ቅድመ ስብሰባ አካሂዷል፡፡ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በአፍሪካ ከ400 ሚሊየን በላይ ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር ይገጥማቸዋል፡፡ በአህጉሪቱ ከ700 ሚሊየን በላይ ዜጎች በተለይም ወጣቶች፣ ሴቶችና የገጠር ነዋሪዎች የንጽህና አጠባበቅ (ሳኒቴሽንና ሀይጅን) ጉድለት ችግር እንደሚያጋጥማቸው ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረትም የአጀንዳ 2063 አንዱ ግብና የዘንድሮው ዓመት መሪ ሀሳብ ያደረገውም ውሃ የዜጎች መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ ነው ብለዋል፡፡ በአህጉሪቷ ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና የአካባቢ ንጽህናን ማረጋገጥ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማስመዝገብ እና ውሃ ወለድ በሽታን ለመከላከል ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ የውሃ ሀብታችን የኢኮኖሚያችን አቅም፣ የህልውናችን መሰረት ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታተ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ትብብር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት ዘላቂ የውሃ ሀብት ልማትን ለማረጋገጥ ተጨባጭ የተግባር ውጤት ማስመዝገቧን ገልጸው፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ተክላለች ብለዋል፡፡ እነዚህ የተተከሉ ችግኞች የፅድቀት መጠንም ከ90 በመቶ በላይ ሲሆን፤ በዚህ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ከፍተኛ መጠን ያለው ውሃ ማዳን እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ እና ተፋሰስ ልማት ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች አፍሪካውያን በትብብር የንጹህ መጠጥ ውሃና ንጽህናን ማረጋገጥ እንደሚችሉ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የወንዝ ዳርቻ እና ኮሪደር ልማት ስራ በአዲስ አበባ ከተማ ጀምራ ወደ ተለያዩ ክልሎች ማስፋቷን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ይህም የወንዞችን ውበትና የውሃ ንጽህናን መጠበቅ አስችሏል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ የገጸ ምድርና ከርሰ ምድር የውሃ ሀብት እንዳይበከል አስፈላጊውን የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ማከናወን እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ በመሆኑም እንደ አፍሪካ በጋራ በመተባበር ከቻልን አንዳችን ለአንዳችን በረከት እንሆናለን፤ ንጹህ የከርሰ ምድር ውሃ ይኖረናልም ብለዋል፡፡
የበልግ አብቃይ የሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ይኖራቸዋል
Feb 9, 2026 159
አዳማ ፤ የካቲት 2/2018 (ኢዜአ)፦በአብዛኛው የበልግ አብቃይ የሀገሪቱ አካባቢዎች መደበኛ እና ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የበጋ ወቅት የአየር ፀባይ ትንበያ ግምገማና የበልግ ወቅት ትንበያ ይፋ ማድረጊያ መድረክ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በአዳማ ማካሄድ ጀምሯል። ኢንስቲትዩቱ በዚሁ መድረክ ላይ ይፋ እንዳደረገው የበልግ ወቅት የአየር ትንበያ በልግ ዋነኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደሚኖራቸው ጠቁሟል። በዚሁ መሰረት የቦረና እና ጉጂ ዞኖች ፣ሲዳማ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ከመደበኛ በላይ ዝናብ ያገኛሉ። እንዳሁም የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል እና የምእራብና ደቡብ ምእራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ደግሞ መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደሚያገኙ ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል። በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት እየተስተዋሉ ከሚገኙ የአየር ሁኔታ ክስተቶች ላይ በመነሳት በሰሜን ምእራብ በመካከለኛው፣ በምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይም መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ይኖራል። በሌላ በኩል የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት መጠን በሰሜን ምስራቅ፣ በሰሜን ምእራብ እና በደቡብ ምእራብ አካባቢዎች ላይ ከመደበኛ በላይ እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች ያመላክታሉ። የበልግ ወቅት የዝናብ አጀማመር በደቡብ አጋማሽ አካባቢዎች ላይ ቀደም ብሎ የሚጀመር ሲሆን በአወጣጥ ረገድ ግን በተወሰኑ ቀናቶች ዘግይቶ ይወጣል ተብሏል። ይህን የዝናብ መጠንና ስርጭት በአግባቡ መጠቀምና በዚህ ወቅት የሚካሄደውን የግብርና እንቅስቃሴ እና ሌሎች ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ስራዎች ከባለሙያዎች ጋር በመመካከር ማከናወን ያስፈልጋል ተብሏል። በዘንድሮ የበልግ ወራት የዝናብ መጠንም ለግብርና ስራ አመቺ መሆኑ ተገልጿል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አጀንዳ 2063: የ50 ዓመቱ የአፍሪካ እቅድ
Feb 13, 2026 158
.አጀንዳ 2063 ‘የምንፈልጋትን አፍሪካ ‘ በሚል መሪ ሀሳብ አፍሪካ ለ50 ዓመት (ከእ.አ.አ 2013 እስከ 2063) የምትመራበትን እቅድ የያዘ ማዕቀፍ ነው። .አጀንዳው ለመጀመሪያ ጊዜ ውይይት የተደረገበት እ.አ.አ በ2013 በአዲስ አበባ በተካሄደው 21ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ(ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት 50ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የተከበረበት ነው)። .አጀንዳ 2063 እ.አ.አ በ2015 በአዲስ አበባ በተካሄደው 24ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ውይይት ተደርጎበት አባል አገራቱ አጽድቀውታል። .የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ አፍሪካ ሕብረት) አፍሪካ ከአፓርታይድ ስርዓት ለማላቀቅና የፖለቲካ ነጻነት እንድታገኝ ሲያደርግ የነበረው ትግል ለአጀንዳ 2063 አጀንዳ መጠንሰስ ምክንያት እንደሆነ ይገለጻል። .አጀንዳ 2063 በአፍሪካ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ የሆነ ልማት ማምጣት እንዲሁም በፓን አፍሪካኒዝምና የአፍሪካ ሕዳሴ ራዕይ ስር አንድነቷን የጠበቀች፣ የራስን እድል በራስ የምትወስን፣ነጻ የሆነች፣የተለወጠችና የበለጸገች አፍሪካ የመፍጠር ግብ እንዳለው የአፍሪካ ሕብረት በድረ ገጹ ላይ ያሰፈረው መረጃ ያሳያል። .አጀንዳ 2063 የአፍሪካን ሁሉን አቀፍና ዘላቂ የልማት ግቦችን ያሳካል ተብሎ የታመነበት የአህጉሪቷ ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ ሲሆን፤አፍሪካን በዓለም መድረክ ተጽእኖ ፈጣሪ የማድረግ ራዕይ ያለው ነው። አጀንዳ 2063 ሰባት ግቦች ሳይሆን ሰባት አላማዎች፣20 ግቦችና 15 ፕሮጀክቶች ያሉት ነው የአጀንዳ 2063 ሰባት አላማዎችና ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫዎች አጀንዳ 2063 ‘የምንፈልጋትን አፍሪካ ‘ በሚል መሪ ሀሳብ አፍሪካ ለ50 ዓመት (ከእ.አ.አ 2013 እስከ 2063) የምትመራበትን እቅድ የያዘ ማዕቀፍ ነው። አጀንዳ 2063 ሰባት አላማዎችና ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫዎች አሉት። እነሱም፦ 1. ሁሉን አቀፍ በሆነ እድገትና ዘላቂ ልማት የበለጸገች አፍሪካን መፍጠር 2. በፓን አፍሪካኒዝም እሳቤዎችና በአፍሪካ ሕዳሴ ራዕይ አማካኝነት የተሳሰረችና ፖለቲካዊ አንድነት ያላት አህጉርን እውን ማድረግ 3. አፍሪካን መልካም አስተዳደር የሰፈነባት፣ የሰብአዊ መብቶችና የሕግ የበላይነት የሚከበርባት፣ ፍትሕ የነገሰባትና ዴሞክራሲያዊ አህጉር ማድረግ 4 .ሰላሟንና አንድነቷን የጠበቀች አፍሪካን መፍጠር 5.ጠንካራ የባህል ማንነት፣ የጋራ ቅርስና እሴቶች ያሏት እንዲሁም ጠንካራ ማህበረሳባዊ የሞራል መሰረት የፈጠረች አፍሪካን ማየት 6. አፍሪካ ልማቷ ዜጎችን ማዕከል ያደረገ፣ የአፍሪካን ሕዝብ በተለይም የወጣቶችና ሴቶችን አቅም የሚጠቀምና ለሕጻናት ክብካቤ ትኩረትን የሰጠ እንዲሆን ማድረግ 7. ጠንካራ፣ አንድነቷን የጠበቀች፣ የማትበገርና በዓለም መድረክ ተጽእኖ ፈጣሪና አጋር የሆነች አፍሪካን መፍጠር ናቸው። የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሄደው 39ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ በአጀንዳ 2063 አፈጻጸም ትግበራ ላይ እንደሚመክር የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
የኮሞሮስ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሶማኒ እና የሌሴቶው ንጉስ ሌትሴ ሳልሳዊ በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገቡ
Feb 11, 2026 142
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2018(ኢዜአ)፦ የኮሞሮስ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሶማኒ እና የሌሴቶው ንጉስ ሌትሴ ሳልሳዊ በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዚዳንቱ እና ንጉሱ ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) እና የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በተያያዘ ዜና የጋምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት መሐመድ ጃሎው በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል። ምክትል ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ አቀባበል አድርገውላቸዋል። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ ይካሄዳል።
48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀመረ
Feb 11, 2026 142
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2018(ኢዜአ)፦ 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ስብሰባው “ዘላቂ የውሃ ኑረትና ንጽህና ስርዓት ለአጀንዳ 2063 ስኬት” በሚል መሪ ሀሳብ ይደረጋል። የአፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ዲፕሎማቶችና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል። በስብሰባው የሚሳተፉ የአፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ሚኒስትር ዴኤታዎች እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል። ምክር ቤቱ በጥር ወር 2018 ዓ.ም 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ በተወያየባቸው አጀንዳዎች ላይ ምክክር ያደርጋል። የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤቱ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል። የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ እስከ ነገ ይቆያል።
የአፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አዲስ አበባ እየገቡ ነው
Feb 11, 2026 125
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2018(ኢዜአ)፦ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በ48ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ እና በ39ኛው የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ እየገቡ ይገኛሉ። ዛሬ ንጋት አዲስ አበባ ከገቡት መካከል የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሙኤል ኦኩድዘቶ አብላካዋ፣ የሲሸልስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባሪ ፏር፣ የሴኔጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቸኪህ ናንግ እና የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ እና አለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ሞንደየሰ ሳሚያ ኩምቢያ ይገኙበታል። በተጨማሪም የኢስዋትኒ የውጭ ጉዳይ እና የአለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ፎሊል ድላሚኒ ሻካንቱ፣ የቶጎ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሮበርት ዱሰይ፣ የታንዛኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የምስራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማህመድ ታቢት ካምቦ እና የላይበሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳራ በይሶሎው ኒያንቲ አዲስ አበባ ገብተዋል። እንዲሁም የኮንጎ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኖይላ ናክዊፓኔ አዬጋናጋቶ በ48ኛው የአፍሪካ ህብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ እና በ39ኛው የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ከገቡት መከካል ይገኙበታል። ሚኒስትሮቹ ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ አቀባበል አድርገውላቸዋል። የሚኒስትሮች የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ለ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል። የጅቡቲ፣ የቻድ፣ የጊኒ ሪፐብሊክ፣ የሌሴቶ፣ የኬንያ፣ አልጄሪያ እና ሞሮኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ትላንት ለሊት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል።
ሐተታዎች
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 516
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 852
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 789
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 1008
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 903
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 847
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 1428
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3728
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3396
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2225
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8029
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6515
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!!
Feb 6, 2026 210
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በያንተስራ ወጋየሁ -ዲላ ቀን ቀንን እየወለደ ጊዜ ሳያቋርጥ እንደ ዥረት መፍሰሱን አያቆምም። ትናንት አዲስ የነበረው አሮጌው የሚባልበት፣ ዛሬ አዲስ ሆኖ ነገ አሮጌ ለመባል ይሮጣል። ወቅቶች ይፈራረቃሉ፣ ይመሻል፣ ይነጋል፣ ትናንት ለዛሬ፣ ዛሬ ለነገ እንዲህ እንዲህ እየተቀባበሉ ዘመን ዘመንን እየተካ ዛሬ ላይ ተደርሷል። በጥምር ግብርናውና በቡናው የሚታወቀው ጌዴኦ ትናንትን ሸኝቶ ዛሬን እንደ አዲስ ለመቀበል ሽር ጉድ እያለ ነው። በክረምቱ የተዘራው ሰብል ተሰብስቦ ወደ ጎተራ እንዳስገባ ጌዴኦ አዲስ ዓመቱን ‹‹ዳራሮ››ን ይቀበላል። ዳራሮ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ቂም የያዘ ቂምና ቁርሾውን የሚተውበት፣ ወጣቶች የሚተጫጩበት፣ አዛውንቶች ወደ ሽምግልና የሚሸጋገሩበት እሴቶችን በውስጡ የያዘ ነው። "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው የጌዴኦ አርሶ አደር ካመረተው ምርት ለመሪው፣ ልጆች ለወላጆችና ለአሳዳጊዎቻቸው፣ አዲስ ተጋቢዎች ለአማቾቻቸው፣ ቂም የያዘ ሰው እንዲሁ የተቀየመውን ሰው ይቅርታ ለመጠየቅ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። "ጉማታ" በጌዴኦ ዘመን መለወጫ ወቅት የሚፈጸም ስጦታ ነው። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማኅበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ነው። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። በዳራሮ በዓል አከባበር ውስጥ "ጉማታ" እጅግ አስፈላጊና ትልቅ ትርጉም ያለው ባህላዊ የክብር ስጦታ የመስጠት ሥርዓት ነው። "ጉማታ" ማለት በቀጥታ ትርጉሙ "ስጦታ" ማለት ቢሆንም፣ በጌዴኦ ባህል ግን ከስጦታ በላይ ነው። ምስጋናን፣ ፍቅርን፣ አክብሮትንና በረከትን የመጋራት መገለጫ ነው። የጌዴአ ባህላዊ የባሌ ስርዓት መሪ ሆነው የሚሰየሙት አባ ገዳ ለህዝብ ከመጸለይ፣ ከማስታረቅና ክፉን በማውገዝ ህዝቡ ተፈጥሮን እንዲንከባከብ ከማስተማር ውጭ አይዘሩም፣ አይነግዱም፣ አልፎም እንሳስትን አያረቡም፡፡ የዳራሮ በዓልን ተከትሎ ህዝቡ የሚያቀርብላቸውን "ጉማታ" በመቀበል ባህላዊ የመሪነት ሚናቸውን በአግባቡ ከመወጣት ውጪ። ኑሮው ከጥምር እርሻ ጋር የተቆራኘው የጌዴኦ ሕዝብ ዘርቶ ካጨደው፣ አርብቶ ካገኘው ከብት፣ አንቦ ከቆረጠው ማር፣ ከሁሉም በአይነት በአይነቱ ሸክፎ ዳራሮ ወደ ሚከበርበት ሶንጎ (አደባባይ) ይተማል። ለጉማታ ከሚቀርቡ ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው ስጦታዎች አንዱ ማር ነው። ማር በጌዴኦ ዘንድ የጣፋጭ ዘመንና የጤና ምልክት ተደርጎ ይወሰዳልና ዋናው ስጦታ ነው። ጌዶኦዎች ቡና፣ ቅቤና ባህላዊ ምግቦች፣ የቁም እንስሳት በግና ስንጋ እንዲሁም ገንዘብ በመያዝ በበዓሉ ውስጥ የጉማታ ስርዓት ሲደርስ ተሽቀዳድመው ለአባ ገዳው በመስጠት ምርቃት ይቀበላሉ። "ጉማታ" የተቀበለው ሰው የሚመርቀው ምርቃት በሰጪው ሕይወት ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይታመናልና ከስጦታው ይልቅ ምርቃቱ ትልቅ ዋጋ አለው። "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው ጌዴኦ በረከትን ማካፈል ለቀጣዩ ዓመት ተጨማሪ በረከት እንደሚያገኝ ስለሚያውቅ ጉማታ መስጠት የዘመናት ቅርሱ ነው። ጉማታ ከአባ ገዳና ከባህል ሽማግሌዎች ባለፈ አርሶ አደሩ ከማጋኖ (ከፈጣሪ) ያገኘውን በረከት ለሚወዳቸውና ለሚያከብራቸው ሰዎች የሚያቀርብበት መንገድ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ገልጸዋል። ልጆች ለወላጆቻቸውና ለቤተሰብ አባላት ላሳደጓቸውና ለሰጧቸው ምርቃት ምስጋናቸውን ለመግለጽ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። በቅርቡ ጋብቻ የመሠረቱ ወጣቶች ወደ አማቾቻቸው ቤት ጉማታ ይዞ በመሄድ ዝምድናቸውን ያጠናክራሉ። በዓመቱ ውስጥ ቅሬታ ወይም ቂም ካለ፣ በዳራሮ ወቅት ጉማታ ይዞ በመሄድ ይቅርታ ይጠየቃል። ጉማታ የሰውን ልብ ለማለስለስና አዲስ ዓመትን በሰላም ለመጀመር ያገለግላል ተብሎ ስለሚታመን። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማህበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ስለመሆኑም ነው ዋና አስተዳዳሪው የጠቆሙት። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። ይህም የመደጋገፍ እሴትን ከማጠናከር በተጓዳኝ ህዝቡ የመንግስት ገቢን እንዲሁም በማህበረሰብ ተሳትፎ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆን መሰረት የጣለ ነው ይላሉ። የዘንድሮው ዳራሮ ከቤት በተለይም ከአባ ገዳው መኖሪያ አንስቶ በሶንጎዎችና በየደረጃው በሚገኙ መዋቅሮች በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ጭምር እየተከበረ መሆኑን ያነሱት አስተዳዳሪው ጉማታም ዋናው የበዓሉ እሴት ሆኖ እየተከበረ ነው ብለዋል። ባህልና ማንነትን በማስጠበቅና በማዳበር፣ ባህሉ ወደ ወጣቶች እንዲተላለፍ በማበረታታት እንዲሁም የጌዴኦ ባህልን ለሌሎች ህዝቦች ለማስተዋወቅና የማህበረሰብ አንድነትና ባህላዊ እሴትን ለማጠናከር እያገለገለ ያለው የጌዴኦ ዘመን መለወጫ ዳራሮ ጥር 29 እና 30 በዲላ ከተማ ይከበራል። የዳራሮ በዓል የጌዴኦን ሕዝብ የሥራ ባህል፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ዕውቀትና የሰላም እሴት ለዓለም የሚያሳይ ትልቅ አጋጣሚ ነው። ይህ በዓል በተለይ የጌዴኦ የባህላዊ መልክዓ ምድር (Cultural Landscape) በዩኔስኮ (UNESCO) በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ተከትሎ፣ አሁን ላይ ከቤትና ከአደባባይ አልፎ ዓለም አቀፋዊ ትኩረት እያገኘ ያለ ታላቅ እሴት ሆኗል። የዓመት ሰው ይበለን!!
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት
Jan 14, 2026 538
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት ብርቱዎች ነገን በማሰብ ሁሌም ታትረው ይሰራሉ፤ ይደክማሉ፤ ይጥራሉ…ለቀጣዩ ትውልድም ጥሪት በማስቀመጥ አሻራቸውን ያኖራሉ። አገር የምትገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው። “አባት ያበጀው፤ ለልጅ ይበጀው” እንደሚባለው ልጆች ከአባቶቻቸው ያገኙትን ጥሪት በአዲስ እውቀትና አሰራር ለአገር እድገት በሚበጅ መልኩ አጠናክረው መጠቀማቸው አይቀርም። “ዕድሜ ጸጋ ነው” የሚለው አባባል አንዳንዴ በዕድሜ ብንገፋም ጠንክረን ከሰራን ብዙ ነገር እናያለን ከሚለው ጋር የተያያዘ ነው። በሰቆጣ ከተማም እድሜ ሳይገድባቸው በልማት ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ለዚህ ማሳያ ናቸው። የከተማዋ ነዋሪ የ67 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ አወቀ እና የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ዕድሜያቸው ቢገፋም ጠንክሮ ከተሰራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና ዕድሜ ጸጋ ሆኖ ብዙ ለውጥ ማየት እንደሚቻል ማሳያ ናቸው። ግለሰቦቹ ከዕድሜ ብዛት ጉልበቴ ደከመ፣ አይኔ ፈዘዘ፣ እጄም ተሳሰረ…ሳይሉ ጊዜያቸውን በደን፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ በማሳለፍ ለወጣቶች የልማት አርአያነት ያለው ተግባር እየፈጸሙ ነው። አቶ ብርሃኑ አወቀ በሰቆጣ ከተማ ዳርቻ የሚገኝ አለቱ ያገጠጠና የተራቆተ አካባቢን ከሌላ አካባቢ ለም አፈር በማምጣትና በመደልደል አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ደን በማልማት ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ነው። ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከወጣሁ ጀምሮ ጠንክሬ በመስራት የምለወጥበትን ሥራ ማሰብ ስነበረብኝ፤ የቆሻሻ መጣያ ሆኖ ለዘመናት የቆየን ጭንጫ መሬት ጠርጌና ደልድዬ ማልማት ችያለሁ ይላሉ ወደኋላ መልስ ብለው የተነሱበትን ሁኔታ ሲያስታውሱ። ግማሽ ሄክታር በማይሞላ መሬት ላይ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ዘይቱና፣ ጌሾ፣ ቡና፣ ማንጎና አቮካዶ አልምተዋል። በተጨማሪም ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመንና ሽንኩርት በማምረት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ጥሪት አፍርተዋል። ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ተግቶ መስራት ከተቻለ ሀብት ማፍራትና ህይወትንም መለወጥ እንደሚቻል የገለጹት አቶ ብርሀኑ፣ ወጣቱም ከእሳቸው የሥራ ትጋት በመማር በአካባቢው ያለውን ፀጋ ለይቶ በማልማት ሊጠቀም ይገባል ሲሉ ይመክራሉ። ሌላው የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ባለፉት 18 ዓመታት በተሰማሩበት የአትክልትና ደን ልማት ሥራ የአካባቢያቸውን ገጽታ ቀይረዋል። የዕድሜ ዘመናቸውን በውትድርናና በመንግስት ሠራተኝነት በማገልገል ሃገራዊ ግዳጃቸውን ሲወጡ ነው የቆዩት። ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከተገለሉ በኋላም ቤት ውስጥ መቀመጥን አልመረጡት። አካፋና ዶማቸውን ይዘው ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ ጌሾ፣ ዘይቱና እና ማንጎ በማልማት ምርቱን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። በአካባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ለይተን ማልማት ከቻልን ድህነትን ማስወገድ የሚከብድ አይሆንም ያሉት አቶ ታደሰ፣ የተራቆተና በጎርፍ የተጎዳን መሬት በማልማት አካባቢውን ሳቢና ማራኪ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት። ወጣቱም ከእሳቸው አርአያነት ያለው ተግባር በመማር በአካባቢው እጁ ላይ ባለ ሀብት ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል በተግባር ማሳየት እንዳለበት መክረዋል። የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ እንደገለጹት፤ በብሔረሰብ አስተዳደሩ 24ሺህ 847 አርሶ አደሮች በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተዋል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል ዕድሜ ሳይገድባቸው ወደ ልማት የገቡ አረጋዊያን እያከናወኑት ያለው የግብርና ልማት ሥራ ለወጣቱ ትልቅ ትምህርት እንደሚሆንም ተናግረዋል። ከእነሱ ልምድ በመውሰድ በዞኑ ወጣቶች፣ ሴቶችና አረጋዊያን በጓሮና ባላቸው መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲያለሙ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ይህም በዞኑ የሚስተዋለውን የስርዓተ ምግብ ችግር ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።