ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ አፍሪካን አንድ በሚያደርጉ አሰባሳቢ አጀንዳዎች በታሪክ የሚዘከር ታላላቅ ሥራዎች እያከናወነች ነው - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Oct 14, 2025 24
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ አፍሪካን አንድ በሚያደርጉ አሰባሳቢ አጀንዳዎች በታሪክ የሚዘከር ታላላቅ ሥራዎች እያከናወነች መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ መመስረት በአፍሪካ በጋራ የመበልጸግ ራዕይን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገልጸዋል። አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ሥራ የጀመረውን ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa - POA) ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የለውጥ ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በጉብኝት መርሃ ግብሩ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶ፣ የምክር ቤቱ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተገኝተዋል። አፈ ጉባኤ ታገሰ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ አፍሪካን አንድ በሚያደርጉ አሰባሳቢ አጀንዳዎች በታሪክ የሚዘከር ትልልቅ ሥራዎችን እያከናወነች ነው። አፍሪካ ባላት አቅም፣ ጥበብና እውቀት ልክ በዓለም ደረጃ አልተዋወቀችም ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ የአፍሪካን እምቅ አቅም የሚያሳይ የሚዲያና ተግባቦት ሥራ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎች ታጥቆ ወደ ሥራ መግባቱ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ጠቁመው፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ገጽታ በማስተዋወቅ ለአፍሪካ ድምጽ ለመሆን ዋነኛ መንገድ ነው ብለዋል። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ በተለያዩ ቋንቋዎች ሥራዎችን ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑን አስታውሰው፤ ለቀጣናዊ ትሥሥር መጠናከር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረውም አብራርተዋል። በቀጣናው ዘላቂ ሠላምና እድገትን እውን ለማድረግ የተደራጀ ሚዲያና ተግባቦት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ መመስረት የጎላ ድርሻ እንደሚኖረው አብራርተዋል። የሚዲያው መመስረት በአፍሪካ በጋራ ለመበልጸግ የተቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወትም ገልጸዋል። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ የሰነቃቸው አህጉራዊ ግቦች እንዲሳኩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ የድሮን ቴክኖሎጂ ምርቶችን ማምረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 14, 2025 31
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ የድሮን ቴክኖሎጂ ምርቶችን ማምረቱን አጠናክሮ መቀጠሉን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በሀገር ውስጥ ማምረት የጀመራቸውን ድሮኖች ምርት በማስፋት የድሮን ቴክኖሎጂን በምርምር እና ሥርፀት ለማሳደግ እንዲሁም ተግባራዊ ተሞክሮን ለማዳበር የሚያግዘውን ትብብር ለመፍጠር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከኢፌዴሪ አየር ኃይል፣ ከመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንደስትሪ ግሩፕ፣ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈራረሙን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ ገልጸዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ በመርሐ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት፥ ብሔራዊ ጥቅምን ከማስከበር እንዲሁም ካለው የላቀ ኢኮኖሚያዊና ስትራቴጂያዊ ፋይዳ አንጻር የድሮን ቴክኖሎጂን በራስ አቅም ማልማት ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ ነው፡፡ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባትም የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ተመርቆ ስራ የጀመረው ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ ለደኅንነት፣ ለመረጃ ስምሪት፣ለሲቪልና ለወታደራዊ አገልግሎቶች የሚውሉ ድሮኖች ምርትን አጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። የድሮን ቴክኖሎጂ በፈጣን ዕድገት ላይ የሚገኝ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሲሳይ፤ እንደ ሀገር ብሔራዊ ጥቅምን ከማስጠበቅ፣ ኢኮኖሚያዊ እድገትን ከማሳለጥ እንዲሁም ወደፊት የሚቃጡ ጥቃቶችን ውጤት ከመወሰን አንፃር ያለውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ በመመዘን በድሮን ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ ገልጿል፡፡ በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆንና በሀገር ውስጥ የተፈጠረውን የድሮን ቴክኖሎጂ ዐቅም ለማጎልበት የአንድ ተቋም እንቅስቃሴ ብቻ በቂ ባለመሆኑ ከአምስቱ ተቋማት ጋር በትብበር እና አጋርነት ለመስራት ስምምነቱ ማስፈለጉን የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ አብራርተዋል፡፡ ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ የሚያመርታቸውን ድሮኖች በዓይነትና በጥራት ለማሳደግ የድሮን ቴክኖሎጂ የሚጠቀማቸውን ስማርት ሴንሰሮች በተመለከተ ከአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አስተዳደር፤ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዘርፉን ምርምር ውጤቶችና የሰለጠነ የሰው ኃይል፤ በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንደስትሪ በኩል ለውጊያ የሚውሉ ድሮኖች የሚታጠቋቸው ጦር መሳሪያዎች ምርትን፤ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የካበተ የአቪዬሽን ዘርፍ ተሞክሮ እንዲሁም ከኢፌዴሪ አየር ኃይል በኩል ተግባራዊ ልምምድ ለመቅሰም ታልሞ የትብበር ስምምነቱ መፈረሙ ተመልክቷል፡፡ ከመግባቢያ ሰነድ ፊርማው በኋላ የስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪና የድሮን ምርቶቹ የተጎበኙ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በዘርፉ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማረጋገጥ እና በሀገር ውስጥ ያሉትን የተለያዩ ተቋማት እና ዩኒቨርሲቲዎች ዕውቀት፣ ልምድና ሀብት በመደመር ውጤታማነትን ለማረጋገጥ በትብብር ለመስራት የወሰደው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘርፉ በሚያደርጋቸው ምርምር እና ልማት እንዲሁም የሰው ኃይልን በማሰልጠን ከስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ ያለውን ተሞክሮ ማካፈል ብቻ ሳይሆን ወደፊት በስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ የሚመረቱ ድሮኖችን መጠቀም የሚችልበት ዕድሎች መኖራቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በዓለማችን ሀገራት ውጥረት ውስጥ በገቡ ጊዜ ሉዓላዊነታቸውን ለማስከበር በሚያካሄዷቸው ማናቸውም ኦፕሬሽኖች ላይ የድሮን ቴክኖሎጂ ሚናው እያደገ መምጣቱን የጠቀሱት የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንደስትሪ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታቸው ሃይለማርያም፤ የሀገራችንን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዘርፉን በራስ አቅም በተገቢው መንገድ ለመጠቀም በትብብር ለመስራት አጋጣሚው ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ አነስተኛ እና መካከለኛ ድሮኖችን በማምረት ስራውን የጀመረ ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ እ.አ.አ በ2030 ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸው ትላልቅ ድሮኖችን በማምረት ለዓለም ገበያ የማቅረብ ራዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደምም ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ስምምነት ፈጽሟል።
ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ሊፈቱ የሚገባው በሁለቱ አገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Oct 14, 2025 34
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙትን የግብጽ አምባሳደር አባይዳ ኤ ኤል ዳንዳራዊን የሹመት ደብዳቤ ዛሬ ተቀብለዋል። ኢዜአ ከፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ፕሬዝዳንቱ ከአምባሳደሩ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ በሁለቱ ሃገራት መካከል ለረጅም ጊዜ የቆየውን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት አንስተዋል። በሁለቱ አገራት መካከል ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ቢኖሩም በሁለቱ ሃገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ የሚደረስባቸው መሆኑንም አስረድተዋል። አገራቱ ግንኙነታቸውን ግብርናን ጨምሮ በኢንዱስትሪ፣ በማኑፋክቸሪንግና በሌሎች በርካታ ዘርፎች መቀጠል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
በሀዲያ ዞን የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የዘርፉን ስኬቶች ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Oct 14, 2025 33
ሆሳዕና፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ በሀዲያ ዞን የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል በዘርፉ እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ፡፡ የዞኑ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል፡፡ በመምሪያው የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ መሰረት አበራ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በዞኑ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡ ለእንስሳት ጤና የሚሆን መኖ ከማዘጋጀት ጀምሮ ዝርያቸውን ለማሻሻል የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በዘርፉ እየተከናወነ ባለው ዘመናዊ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል። የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ዮሐንስ በበኩላቸው በከተማው የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል ከወተት ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ባለፈው ዓመት በተከናወነው የእንስሳት ዝርያ የማሻሻል ስራን 82 በመቶ ላይ ማድረስ መቻሉን ጠቅሰው፤ በዚህም የወተት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በተከናወነው ስራ አበረታች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡ በሆሳዕና ከተማ በሊች አምባ ቀበሌ በእንስሳት እርባታ ላይ የተሰማሩት አቶ ዳንኤል ብርሃኑ እና በከተማው የሄጦ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ግርማ ቲርካሶ፤ መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ በሰጠው ትኩረት የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ትግበራው ውጤታማ እያደረገን ነው ብለዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና አርሶ አደሮች ተገኝተዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ የወጪ ንግድ አፈፃፀሙን ቀጣይነት እንዲኖረው አድርጓል
Oct 14, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የወጪ ንግድ አፈፃፀሙን ከፍተኛ ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት እንዲኖረው ማድረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ ተካሂዷል፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በሩብ ዓመቱ በዋና ዋና ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በሩብ ዓመቱ በወጪ ንግድ አፈጻጸም፣ በኦንላይን ንግድ ምዝገባ፣ በድህረ ፈቃድ ቁጥጥር፣ በዓለም የንግድ ድርጅት ድርድር እንዲሁም የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን በማስጀመር እመርታዊ ለውጥ ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት የወጪ ንግድን በዓይነት፣ በመጠንና በገቢ በማሳደግ፣ ዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር አስተማማኝ የገበያ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ግብ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል፡፡ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ክረምት እንደመሆኑ ለንግዱ ማህበረሰብ ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት አስቸጋሪ መሆኑን አንስተዋል። ይሁን እንጂ በበጀት ዘመኑ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከወጪ ንግድ ከ 2 ነጥብ 48 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል ብለዋል፡፡ የወጪ ንግድ አፈፃፀምን በተመለከተ በኩራት መናገር የሚቻልበት መሆኑን ገልጸው፤ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 65 በመቶ ብልጫ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ የተመዘገበው ውጤት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 980 ሚሊዬን ዶላር ብልጫ እንዳለው ጠቅሰው፤ በበጀት ዓመቱ የታቀደውን 9 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ማሳካት እንደሚቻል ያሳያል ብለዋል፡፡ ይሄውም የኢትዮጵያ የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የወጪ ንግድ አፈፃፀሙን ከፍተኛ ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ማድረጉን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከኦንላይን ንግድ ምዝገባ ከ980 ሺህ በላይ የንግድ ፈቃድ ምዝገባና ዕድሳት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ የኦንላይን ንግድ ምዝገባ 141 በመቶ አፈፃፀም መመዝገቡን በማንሳት፤ በበጀት ዓመቱ ማጠናቀቂያ የታቀደውን ሶስት ሚሊዬን ማሳካት እንደሚቻል ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነትን ለማሳካት 6ኛው የሥራ ላይ የቡድን ስብሰባ ያደረገችበት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ከስድስት ሀገራት ጋር ውጤታማ የሁለትዮሽ የገበያ ድርድር መደረጉን ተናግረዋል። ከሌሎች ሀገራት ጋርም ቀልጣፋ ድርድር እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው፤ ድርድሩ እንደሚሳካ ተስፋ ሰጭ ምልክቶች እየታዩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የብዙዎች ጥያቄ የነበረውን የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ትግበራ በአየርና በየብስ ትራንስፖርት መጀመር መቻሉን ተናግረዋል፡፡ አጠቃላይ ሩብ ዓመቱ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ተጠናክሮ የቀጠለበት መሆኑን ጠቁመው፤ አፈጻጸሙ በኢትዮጵያ ልክ ለመድረስ ከዚህ በላይ መስራት እንዳለብን አሳይቶናል ብለዋል፡፡
ፖለቲካ
ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ሊፈቱ የሚገባው በሁለቱ አገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Oct 14, 2025 34
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙትን የግብጽ አምባሳደር አባይዳ ኤ ኤል ዳንዳራዊን የሹመት ደብዳቤ ዛሬ ተቀብለዋል። ኢዜአ ከፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ፕሬዝዳንቱ ከአምባሳደሩ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ በሁለቱ ሃገራት መካከል ለረጅም ጊዜ የቆየውን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት አንስተዋል። በሁለቱ አገራት መካከል ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ቢኖሩም በሁለቱ ሃገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ የሚደረስባቸው መሆኑንም አስረድተዋል። አገራቱ ግንኙነታቸውን ግብርናን ጨምሮ በኢንዱስትሪ፣ በማኑፋክቸሪንግና በሌሎች በርካታ ዘርፎች መቀጠል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ
Oct 14, 2025 77
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ዛሬ ተቀበሉ። ፕሬዚዳንቱ ዛሬ በብሔራዊ ቤተ መንግስት በተካሄደው ሥነ ስርዓት ላይ የተለያዩ አገራትን አዳዲስ አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀብለዋል። ለፕሬዚዳንት ታዬ የሹመት ደብዳቤያቸወን ካቀረቡት መካከል የሞሪታኒያ አምባሳደር ኢል ሀውሴን ኦልድ ናጊ፣የካዛኪስታን አምባሳደር ዣልጋስ አዲልባየቭ ፣ የቫቲካን አምባሳደር ብሬን ኦዲጊግዊ፣የባንግላዲሽ አምባሳደር ኤር ቫይስ ማርሻል ሲትዋት ናዬም እና የዐረብ ሊግ አምባሳደር መሐመድ ኦማር አል ማርሆን ይጠቀሳሉ። በተመሳሳይ የኢንዶኔዥያው አምባሳደር ፋይዝል ቸሪይ ሲዳርት፣ የሰርቢያ አምባሳደር ዳቮር ትርኩልጃ እና የስዊድኑ አምባሳደር ማኙስ ሌናርትሶን የሹመት ደብዳቤያቻውን አቅርበዋል። በተጨማሪም የካናዳው አምባሳደር ኒኮላስ ሲማርድ፣ ሲውዘርላንድ አምባሳድር ሪካረድ ቻንዳ፣ የግብጹ አምባሳደር ኦባይዳ ኢል ዳንዳራውይ፣ የሀንጋሪው አምባሳደር አቲላ ቶዝ፣ ሳን ማሪያኖ አምባሳደር ፔሮ ስካርፔሊኒ እና የቱሪክሜንስታን አምባሳደር መካን ኢሻነጉሊየብ የሹመት ደብዳቤያቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለአምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የስራ መመሪያ ሰጡ
Oct 14, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ለተመደቡት አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን ተመድበዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን ከፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በመቀበል በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መኃላ ፈፅመዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለአምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ እና ጅቡቲን ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ የሥራ መመሪያ መስጠታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ ተገኝተዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) ከዚህ ቀደም የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ሆነው ማገልገላቸው ይታወቃል።
የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ-ከንቲባ ከድር ጁሃር
Oct 14, 2025 76
ድሬዳዋ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። የአስተዳደሩ የሴክተሮችና የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች የመጀመሪያ ሩብ በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እየተገመገመ ይገኛል። በግምገማ መድረኩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንዳሉት በከተማ አስተዳደሩ የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት የተተገበሩ የልማት እቅዶች አበረታች ውጤት አስገኝተዋል። በተለይ መንግስታዊ አገልግሎቶችን ፈጣን ለማድረግ በተሰራው ሥራ ለተገኘው ውጤት የድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የራሱ ድርሻ እንዳለው አክለዋል። የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በቅንጅት የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ከንቲባ ከድር አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ የአስተዳደሩን የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም እንዲሁም የሴክተሮችና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የዕቅድ ክንውን ሪፖርትን የአስተዳደሩ የፕላንና ኢኮኖሚ ልማት ኮሚሽነር ኃይለማርያም ዳዲ አቅርበዋል። በሪፖርቱም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ገቢን በአግባቡ ለመሰብሰብ በተደረገ ጥረት ከታክስና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች 1 ነጥብ 76 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል። የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት በቅዳሜና እሁድ ገበያ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህዝብ እንዲቀርቡ ለማድረግ መቻሉንም ኮሚሽነሩ አንስተዋል። የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስም ስምንት የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት መጀመራቸውን ነው የገለጹት። በተጨማሪም በገጠርና በከተማ ከ6 ሺህ 280 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት ማስገኘታቸውን አመልክተዋል።
ለክልሉ ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራ ውጤታማነት የምክር ቤቱ የክትትልና ቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 14, 2025 120
ቴፒ፣ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የምክር ቤቱ የክትትልና ቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አስታወቀ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት በ3ኛ ዓመት 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በማካሄድ የአዲስ አፈ ጉባኤ ሹመትም አጽድቋል። የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ በመሆን የተሾሙት አቶ ጌታቸው ኬኒ፤ በስራ ጊዜያቸው አስፈፃሚውን አካል የመደገፍ፣ የመከታተልና የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚሰሩ መሆኑን አረጋግጠዋል። ለክልሉ ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራ ውጤታማነት የምክር ቤቱ የክትትልና ቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል። የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ መሰለ ከበደ፤ በበኩላቸው ምክር ቤቱ በክልሉ ብሎም እንደ ሀገር እየተከናወኑ ባሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ጥረቶች ላይ የድርሻውን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል። በሀገሪቱ ሰላምን በማጽናት እንዲሁም ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጎልበት ረገድ ብዙ ስለመሰራቱ አስታውሰው በዚህ ረገድ የምክር ቤቱ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
አቶ ሳንዶካን ደበበ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ
Oct 14, 2025 155
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቶ ሳንዶካን ደበበን የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርገው ሾመዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አቶ ሳንዶካን ደበበ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርገው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 49ኛ መደበኛ ስብሰባ በኮሚሽኑ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ በመወያየት ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ጉዞ ዓለም በሚያየውና በሚመሰክረው ሀገራዊ ስኬት የተደገፈ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Oct 13, 2025 229
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየው፣ በሚዳስሰውና በሚመሰክርላቸው ስኬቶች የተደገፈ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ። 18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ’’ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነትና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል። በዚሁ ወቅት ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፤ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ፍቅር፣ ክብርና ቃል ኪዳን በልባቸው የሚያድሱበት የጋራ ማንነታቸውን የሚያጎለብቱበትና የነገ ተስፋን የሚያጸኑበት ነው ብለዋል። ክብረ በዓሉ ያለፈውን የጀግንነት ገድል፣ የዛሬውን የልማት ጥረት፣ የነገውን የዕድገትና ብልጽግና ትልም በማጣመር ፈጣን ዕድገት ለምታስመዘግበው ኢትዮጵያ ድል አብሳሪና የጉዞ ህያው ምስክር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን የህልውና ፈተናዎች በህዝቦቿ የአንድነት ብርቱ ክንድ በጽናት ተሻግራ የራሷን ዕድል የመወሰን ብቃት እያስመሰከረች መሆኗንም አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየውና በሚዳስሰው ብሎም በሚመሰክርላቸው ሀገራዊ ስኬቶች የተደገፈ ነው ብለዋል። የዚህ ብስራት መቅረዝና ከፍታም የዘመናት ህልም የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ የሀገርንና ቀጣናዊ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪ የደም ስር ለመሆን መብቃቱን ገልጸዋል። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ከብርሃን ምንጭነት ባሻገር ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሲቆሙ ታላላቅ ሀገራዊ የልማት ገድሎችን ማስመዝገብ እንደሚቻል በተግባር የተረጋገጠበት የሉዓላዊነት ማህተም መሆኑን ተናግረዋል። በአረንጓዴ ዐሻራም በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች መትከሏን አስታውሰው፤ ይህም የኢትዮጵያን ገጽታ በመቀየርና ለዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ በማበርከት ዓለም አቀፍ ከበሬታና ሞገስ ያስገኘላት የልማት ገድል ነው ብለዋል። የዕድገት ጉዟችን ቀጣይ ምዕራፍ የኢኮኖሚ ብርታትን ማረጋገጥ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታውም በግብርና ምርታማነት የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከውጭ ከሚገባ የማዳበሪ ጥገኝነት በማላቀቅ ሀገራዊ ኢኮኖሚን የሚያጠናክር ታላቅ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ጋዝ ሃብትን በመጠቀም ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለኃይል ምንጭነት እንዲውል የማድረግ ውጥንም በአዲስ የኃይል ምንጭ የኢኮኖሚ ዕድገትና ብልጽግና ጉዞን እንደሚያፋጥን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ለወጣቶች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩና የሀገርን የከፍታ ዘመን በማይናወጥ መሠረት ለማስቀመጥ እንደሚረዱ ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ውጤታማነት ለማስቀጠልም በልዩነት ውስጥ ያለን ወርቃማ ውበት በማክበር የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ዘላቂ ሰላም መሠረት እየጣለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የሚከበረው በጠንካራ አንድነትና በበለጸገ ኢኮኖሚ ላይ ማቆም ሲቻል እንደሆነም አስገንዝበዋል። ለዚህም ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ትብብር ላይ የተመሰረተ ፍትሐዊ የባሕር በር የማግኘትና የመጠቀም መብታችን በሰላማዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና በሰጥቶ መቀበል መርህ ማስከበራችን ይቀጥላል ብለዋል። ኢትዮጵያውያንም በአዕምሯቸው ሰላምን በማጽናት በልባቸው የተስፋ ወጋገን አጥብቆ በመያዝ በክንዳቸው ብርታትም ሠንደቅ ዓላማና ሀገራቸውን መጠበቅ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።
የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ ይገባል
Oct 13, 2025 145
አርባ ምንጭ፣ዲላ፣ ቦንጋ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ) :- የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንደሚገባ ተመላከተ። 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሐሳብ በቦንጋ፣ ዲላና አርባ ምንጭ ከተሞች በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል። በቦንጋ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ላይ መልእክት ያስተላለፉት የካፋ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ግርማ ደፋር የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ስናከብር በየዘመኑ ለሀገር ነፃነትና ክብር የተከፈለውን ዋጋ በማሰብ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር ሉዓላዊነትና የነፃነት ምልክት መሆኑን ጠቅሰው ክብሩን በሚመጥን የስራ ትጋት በርትቶ በመስራት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገር ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ሰነድ ያቀረቡት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ንጉሴ ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው ለሰንደቅ ዓላማ ከፍታ የተከፈለው ዋጋ የማይረሳና በየዘመኑ እየተዘከረ የሚኖር መሆኑን ገልፀዋል። የቀኑ መከበር ሀገራዊ እሴቶችን አጠናክሮ ለትውልድ በማስተላለፍ አንድነታችንንና ህብረታችንን በማጠናከር ህብረ-ብሔራዊነትን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፣ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ምልክትና የሉዓላዊነት መገለጫ መሆኑን አንስተው ቀኑ ከሌሎች በዓላት በተለየ መልኩ በሰፊው መከበር እንዳለበት አንስተዋል። በአርባ ምንጭ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወላይቴ ቢቶ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር መለያ፣ የሉዓላዊነትና የአንድነታችን መገለጫ ነው ብለዋል፡፡ የሃገሪቱን የማንሠራራት ጉዞ ለማስቀጠልም ሁሉም በተሰማራበት መስክ ሰንደቅ ዓላማን ከፍ የሚያደርግ ተግባር መፈጸም እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ በተመሳሳይም በዲላ ከተማ በዓሉ ሲከበር የጌዴኦ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ምስጋና ዋቃዮ እንዳሉት ቀኑ ህገ መንግስታዊ መሰረት ያለውና ህብረተሰቡን በቅንነት ለማገልገል ዳግም ቃላችንን የምናድስበት ነው። የህብረ ብሔራዊትንና ሉዓላዊነት መገለጫ የሆነውን ሰንደቅ ዓላማ ማክበርና ማጉላት እንደሚገባም አመልክተዋል። ሰንደቅ ዓላማ የሃገራችን ኩራትና ነጻነት በመሆኑ የሚገባውን ክብር ልንሰጠው ይገባል ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጠቅ ዶሪ በተሰማራንበት ዘርፍ ውጤታማ በመሆን የሰንደቅ ዓላማ ክብርን ማጎልበት እንደሚገባም አንስተዋል።
ፖለቲካ
ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ሊፈቱ የሚገባው በሁለቱ አገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Oct 14, 2025 34
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙትን የግብጽ አምባሳደር አባይዳ ኤ ኤል ዳንዳራዊን የሹመት ደብዳቤ ዛሬ ተቀብለዋል። ኢዜአ ከፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ፕሬዝዳንቱ ከአምባሳደሩ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ በሁለቱ ሃገራት መካከል ለረጅም ጊዜ የቆየውን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት አንስተዋል። በሁለቱ አገራት መካከል ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ቢኖሩም በሁለቱ ሃገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ የሚደረስባቸው መሆኑንም አስረድተዋል። አገራቱ ግንኙነታቸውን ግብርናን ጨምሮ በኢንዱስትሪ፣ በማኑፋክቸሪንግና በሌሎች በርካታ ዘርፎች መቀጠል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ
Oct 14, 2025 77
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ዛሬ ተቀበሉ። ፕሬዚዳንቱ ዛሬ በብሔራዊ ቤተ መንግስት በተካሄደው ሥነ ስርዓት ላይ የተለያዩ አገራትን አዳዲስ አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀብለዋል። ለፕሬዚዳንት ታዬ የሹመት ደብዳቤያቸወን ካቀረቡት መካከል የሞሪታኒያ አምባሳደር ኢል ሀውሴን ኦልድ ናጊ፣የካዛኪስታን አምባሳደር ዣልጋስ አዲልባየቭ ፣ የቫቲካን አምባሳደር ብሬን ኦዲጊግዊ፣የባንግላዲሽ አምባሳደር ኤር ቫይስ ማርሻል ሲትዋት ናዬም እና የዐረብ ሊግ አምባሳደር መሐመድ ኦማር አል ማርሆን ይጠቀሳሉ። በተመሳሳይ የኢንዶኔዥያው አምባሳደር ፋይዝል ቸሪይ ሲዳርት፣ የሰርቢያ አምባሳደር ዳቮር ትርኩልጃ እና የስዊድኑ አምባሳደር ማኙስ ሌናርትሶን የሹመት ደብዳቤያቻውን አቅርበዋል። በተጨማሪም የካናዳው አምባሳደር ኒኮላስ ሲማርድ፣ ሲውዘርላንድ አምባሳድር ሪካረድ ቻንዳ፣ የግብጹ አምባሳደር ኦባይዳ ኢል ዳንዳራውይ፣ የሀንጋሪው አምባሳደር አቲላ ቶዝ፣ ሳን ማሪያኖ አምባሳደር ፔሮ ስካርፔሊኒ እና የቱሪክሜንስታን አምባሳደር መካን ኢሻነጉሊየብ የሹመት ደብዳቤያቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለአምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የስራ መመሪያ ሰጡ
Oct 14, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ለተመደቡት አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን ተመድበዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን ከፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በመቀበል በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መኃላ ፈፅመዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለአምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ እና ጅቡቲን ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ የሥራ መመሪያ መስጠታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ ተገኝተዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) ከዚህ ቀደም የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ሆነው ማገልገላቸው ይታወቃል።
የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ-ከንቲባ ከድር ጁሃር
Oct 14, 2025 76
ድሬዳዋ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። የአስተዳደሩ የሴክተሮችና የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች የመጀመሪያ ሩብ በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እየተገመገመ ይገኛል። በግምገማ መድረኩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንዳሉት በከተማ አስተዳደሩ የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት የተተገበሩ የልማት እቅዶች አበረታች ውጤት አስገኝተዋል። በተለይ መንግስታዊ አገልግሎቶችን ፈጣን ለማድረግ በተሰራው ሥራ ለተገኘው ውጤት የድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የራሱ ድርሻ እንዳለው አክለዋል። የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በቅንጅት የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ከንቲባ ከድር አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ የአስተዳደሩን የ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም እንዲሁም የሴክተሮችና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የዕቅድ ክንውን ሪፖርትን የአስተዳደሩ የፕላንና ኢኮኖሚ ልማት ኮሚሽነር ኃይለማርያም ዳዲ አቅርበዋል። በሪፖርቱም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ገቢን በአግባቡ ለመሰብሰብ በተደረገ ጥረት ከታክስና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች 1 ነጥብ 76 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል። የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት በቅዳሜና እሁድ ገበያ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህዝብ እንዲቀርቡ ለማድረግ መቻሉንም ኮሚሽነሩ አንስተዋል። የህዝብን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስም ስምንት የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት መጀመራቸውን ነው የገለጹት። በተጨማሪም በገጠርና በከተማ ከ6 ሺህ 280 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት ማስገኘታቸውን አመልክተዋል።
ለክልሉ ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራ ውጤታማነት የምክር ቤቱ የክትትልና ቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 14, 2025 120
ቴፒ፣ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የምክር ቤቱ የክትትልና ቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አስታወቀ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት በ3ኛ ዓመት 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በማካሄድ የአዲስ አፈ ጉባኤ ሹመትም አጽድቋል። የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ በመሆን የተሾሙት አቶ ጌታቸው ኬኒ፤ በስራ ጊዜያቸው አስፈፃሚውን አካል የመደገፍ፣ የመከታተልና የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚሰሩ መሆኑን አረጋግጠዋል። ለክልሉ ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራ ውጤታማነት የምክር ቤቱ የክትትልና ቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል። የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ መሰለ ከበደ፤ በበኩላቸው ምክር ቤቱ በክልሉ ብሎም እንደ ሀገር እየተከናወኑ ባሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ጥረቶች ላይ የድርሻውን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል። በሀገሪቱ ሰላምን በማጽናት እንዲሁም ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጎልበት ረገድ ብዙ ስለመሰራቱ አስታውሰው በዚህ ረገድ የምክር ቤቱ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
አቶ ሳንዶካን ደበበ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ
Oct 14, 2025 155
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቶ ሳንዶካን ደበበን የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርገው ሾመዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አቶ ሳንዶካን ደበበ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርገው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 49ኛ መደበኛ ስብሰባ በኮሚሽኑ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ በመወያየት ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ጉዞ ዓለም በሚያየውና በሚመሰክረው ሀገራዊ ስኬት የተደገፈ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
Oct 13, 2025 229
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየው፣ በሚዳስሰውና በሚመሰክርላቸው ስኬቶች የተደገፈ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ። 18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ’’ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነትና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል። በዚሁ ወቅት ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፤ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ፍቅር፣ ክብርና ቃል ኪዳን በልባቸው የሚያድሱበት የጋራ ማንነታቸውን የሚያጎለብቱበትና የነገ ተስፋን የሚያጸኑበት ነው ብለዋል። ክብረ በዓሉ ያለፈውን የጀግንነት ገድል፣ የዛሬውን የልማት ጥረት፣ የነገውን የዕድገትና ብልጽግና ትልም በማጣመር ፈጣን ዕድገት ለምታስመዘግበው ኢትዮጵያ ድል አብሳሪና የጉዞ ህያው ምስክር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን የህልውና ፈተናዎች በህዝቦቿ የአንድነት ብርቱ ክንድ በጽናት ተሻግራ የራሷን ዕድል የመወሰን ብቃት እያስመሰከረች መሆኗንም አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ጉዞ በምኞት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ዓለም በሚያየውና በሚዳስሰው ብሎም በሚመሰክርላቸው ሀገራዊ ስኬቶች የተደገፈ ነው ብለዋል። የዚህ ብስራት መቅረዝና ከፍታም የዘመናት ህልም የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ የሀገርንና ቀጣናዊ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪ የደም ስር ለመሆን መብቃቱን ገልጸዋል። ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ከብርሃን ምንጭነት ባሻገር ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሲቆሙ ታላላቅ ሀገራዊ የልማት ገድሎችን ማስመዝገብ እንደሚቻል በተግባር የተረጋገጠበት የሉዓላዊነት ማህተም መሆኑን ተናግረዋል። በአረንጓዴ ዐሻራም በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች መትከሏን አስታውሰው፤ ይህም የኢትዮጵያን ገጽታ በመቀየርና ለዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ በማበርከት ዓለም አቀፍ ከበሬታና ሞገስ ያስገኘላት የልማት ገድል ነው ብለዋል። የዕድገት ጉዟችን ቀጣይ ምዕራፍ የኢኮኖሚ ብርታትን ማረጋገጥ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታውም በግብርና ምርታማነት የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሚስችል መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከውጭ ከሚገባ የማዳበሪ ጥገኝነት በማላቀቅ ሀገራዊ ኢኮኖሚን የሚያጠናክር ታላቅ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ጋዝ ሃብትን በመጠቀም ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለኃይል ምንጭነት እንዲውል የማድረግ ውጥንም በአዲስ የኃይል ምንጭ የኢኮኖሚ ዕድገትና ብልጽግና ጉዞን እንደሚያፋጥን አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ለወጣቶች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩና የሀገርን የከፍታ ዘመን በማይናወጥ መሠረት ለማስቀመጥ እንደሚረዱ ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ውጤታማነት ለማስቀጠልም በልዩነት ውስጥ ያለን ወርቃማ ውበት በማክበር የሀገራዊ ምክክር ሂደት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ዘላቂ ሰላም መሠረት እየጣለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የሚከበረው በጠንካራ አንድነትና በበለጸገ ኢኮኖሚ ላይ ማቆም ሲቻል እንደሆነም አስገንዝበዋል። ለዚህም ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ትብብር ላይ የተመሰረተ ፍትሐዊ የባሕር በር የማግኘትና የመጠቀም መብታችን በሰላማዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና በሰጥቶ መቀበል መርህ ማስከበራችን ይቀጥላል ብለዋል። ኢትዮጵያውያንም በአዕምሯቸው ሰላምን በማጽናት በልባቸው የተስፋ ወጋገን አጥብቆ በመያዝ በክንዳቸው ብርታትም ሠንደቅ ዓላማና ሀገራቸውን መጠበቅ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።
የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ ይገባል
Oct 13, 2025 145
አርባ ምንጭ፣ዲላ፣ ቦንጋ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ) :- የሰንደቅ ዓላማውን ክብር በሚመጥን የስራ ትጋት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እንደሚገባ ተመላከተ። 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሐሳብ በቦንጋ፣ ዲላና አርባ ምንጭ ከተሞች በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል። በቦንጋ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ላይ መልእክት ያስተላለፉት የካፋ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ግርማ ደፋር የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ስናከብር በየዘመኑ ለሀገር ነፃነትና ክብር የተከፈለውን ዋጋ በማሰብ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር ሉዓላዊነትና የነፃነት ምልክት መሆኑን ጠቅሰው ክብሩን በሚመጥን የስራ ትጋት በርትቶ በመስራት የበለፀገችና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀች ሀገር ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ብለዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ሰነድ ያቀረቡት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ንጉሴ ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው ለሰንደቅ ዓላማ ከፍታ የተከፈለው ዋጋ የማይረሳና በየዘመኑ እየተዘከረ የሚኖር መሆኑን ገልፀዋል። የቀኑ መከበር ሀገራዊ እሴቶችን አጠናክሮ ለትውልድ በማስተላለፍ አንድነታችንንና ህብረታችንን በማጠናከር ህብረ-ብሔራዊነትን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፣ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ምልክትና የሉዓላዊነት መገለጫ መሆኑን አንስተው ቀኑ ከሌሎች በዓላት በተለየ መልኩ በሰፊው መከበር እንዳለበት አንስተዋል። በአርባ ምንጭ ከተማ በተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወላይቴ ቢቶ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር መለያ፣ የሉዓላዊነትና የአንድነታችን መገለጫ ነው ብለዋል፡፡ የሃገሪቱን የማንሠራራት ጉዞ ለማስቀጠልም ሁሉም በተሰማራበት መስክ ሰንደቅ ዓላማን ከፍ የሚያደርግ ተግባር መፈጸም እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ በተመሳሳይም በዲላ ከተማ በዓሉ ሲከበር የጌዴኦ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ምስጋና ዋቃዮ እንዳሉት ቀኑ ህገ መንግስታዊ መሰረት ያለውና ህብረተሰቡን በቅንነት ለማገልገል ዳግም ቃላችንን የምናድስበት ነው። የህብረ ብሔራዊትንና ሉዓላዊነት መገለጫ የሆነውን ሰንደቅ ዓላማ ማክበርና ማጉላት እንደሚገባም አመልክተዋል። ሰንደቅ ዓላማ የሃገራችን ኩራትና ነጻነት በመሆኑ የሚገባውን ክብር ልንሰጠው ይገባል ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጠቅ ዶሪ በተሰማራንበት ዘርፍ ውጤታማ በመሆን የሰንደቅ ዓላማ ክብርን ማጎልበት እንደሚገባም አንስተዋል።
ማህበራዊ
ኢትዮጵያ አፍሪካን አንድ በሚያደርጉ አሰባሳቢ አጀንዳዎች በታሪክ የሚዘከር ታላላቅ ሥራዎች እያከናወነች ነው - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Oct 14, 2025 24
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ አፍሪካን አንድ በሚያደርጉ አሰባሳቢ አጀንዳዎች በታሪክ የሚዘከር ታላላቅ ሥራዎች እያከናወነች መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ መመስረት በአፍሪካ በጋራ የመበልጸግ ራዕይን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገልጸዋል። አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ሥራ የጀመረውን ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa - POA) ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የለውጥ ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በጉብኝት መርሃ ግብሩ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶ፣ የምክር ቤቱ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተገኝተዋል። አፈ ጉባኤ ታገሰ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ አፍሪካን አንድ በሚያደርጉ አሰባሳቢ አጀንዳዎች በታሪክ የሚዘከር ትልልቅ ሥራዎችን እያከናወነች ነው። አፍሪካ ባላት አቅም፣ ጥበብና እውቀት ልክ በዓለም ደረጃ አልተዋወቀችም ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ የአፍሪካን እምቅ አቅም የሚያሳይ የሚዲያና ተግባቦት ሥራ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎች ታጥቆ ወደ ሥራ መግባቱ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ጠቁመው፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ገጽታ በማስተዋወቅ ለአፍሪካ ድምጽ ለመሆን ዋነኛ መንገድ ነው ብለዋል። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ በተለያዩ ቋንቋዎች ሥራዎችን ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑን አስታውሰው፤ ለቀጣናዊ ትሥሥር መጠናከር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረውም አብራርተዋል። በቀጣናው ዘላቂ ሠላምና እድገትን እውን ለማድረግ የተደራጀ ሚዲያና ተግባቦት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ መመስረት የጎላ ድርሻ እንደሚኖረው አብራርተዋል። የሚዲያው መመስረት በአፍሪካ በጋራ ለመበልጸግ የተቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወትም ገልጸዋል። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ የሰነቃቸው አህጉራዊ ግቦች እንዲሳኩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
ለጋራ ትርክት ግንባታና ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ሚናችንን ይበልጥ እናጠናክራለን- የሚዲያና ኮሙኒኬሽን አካላት
Oct 14, 2025 37
ቦንጋ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፡- ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ለሚያጎለብቱ የጋራ ትርክት ግንባታና ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ሚናቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን አካላት ገለጹ። "በአጋርነት የዳበረ ኮሙኒኬሽን፤ ለሕዝብ እምነትና ለሀገር ብልጽግና" በሚል መሪ ሀሳብ ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ አካላት የተዘጋጀ የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሄዷል ። ከተሳታፊዎቹ መካከል የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትዎርክ ምክትል ስራ አስኪያጅ ካሳሁን ወዳጆ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ሀገሪቱ የተያያዘችውን ሁሉን አቀፍ የብልፅግና ጉዞ በማሳካት ሂደት ውስጥ ትልቅ ድርሻ አለው። በተለይም ለብሔራዊ ጥቅም መከበርና ለጋራ ትርክት ግንባታ ዘርፉ ቀዳሚ አጀንዳ አድርጎ እንዲሰራ ሚናቸውን ይበልጥ እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የዋካ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ወንድሙ ዋኮ፤ በተለያዩ ቋንቋዎች ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትንና የጋራ ትርክት ግንባታን የሚያጠናክሩ መረጃዎችን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ሚናቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። በክልሉ የሚገኙ ፀጋዎችን በተገቢው የማስተዋወቅ ኃላፊነታቸውን በቁርጠኝነት እንደሚወጡ የገለፁት ደግሞ የቤንች ሸኮ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ባለሙያ እየሩሳሌም አለሙ ናቸው። ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለሕብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ የጋራ ትርክት ለማስረፅና ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጎልበት ጭምር እንደሚሰሩም ገልጸዋል። በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መብራቱ መርክኔ፤ ለብልፅግና የሚተጋና ለሕዝብ ታማኝ የሆነ የሚዲያ ባለሙያና አመራር መፍጠር አስፈላጊ ነው ብለዋል። ዘርፉ ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ጭምር ኃላፊነቱን መወጣት እንደሚጠበቅበትም ተናግረዋል። የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ አለሙ፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎች ብሔራዊ ትርክትን የሚያጠናክሩ፣ አብሮነትን የሚያጎለብቱና የሀገር ብልፅግናን የሚያሳልጡ መሆን እንዳለባቸው አብራርተዋል። በመድረኩ ማጠቃለያም የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የዘርፉ አካላት የማበረታቻ ሽልማትና እውቅና ተሰጥቷል።
በአፍሪካ የመድሀኒት አቅርቦትን በራስ አቅም ለመሸፈን የጋራ ጥረትና አቅምን ማጎልበት ያስፈልጋል- ዶክተር መቅደስ ዳባ
Oct 14, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦በአፍሪካ የመድሀኒት አቅርቦትን በራስ አቅም ለመሸፈን የጋራ ጥረትና አቅምን ማጎልበት እንደሚያስፈልግ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የጤና ሚኒስቴር ከአፍሪካ የበሽታ ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የአፍሪካ የመድሀኒት ግዢ ማዕቀፍ ላይ ያተኮረ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። ከዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ውይይት የአፍሪካ ሀገራት የመድሀኒት አቅራቢ ተቋማትና የሚመለከታቸው አካላት ያላቸውን ልምድ የሚጋሩበት ነው። በዚህ ወቅት የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ እንዳሉት የህክምና ግብዓት አቅርቦትን ለማረጋገጥ ጠንካራ የግዢና ቁጥጥር ስርዓትን መዘርጋት ይጠይቃል። በተለይ ከኮቪድ 19 መከሰት በኋላ ሀገራት የህክምና ግብዓት አቅርቦትን በራስ አቅም ለመሸፈን የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ ትልቅ አቅም ያላት መሆኑን አንስተው በአህጉሪቱ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን አቅም ማጎልበት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የመድሃኒት አቅርቦት ግዢ ስርዓትን ለማሳለጥ የህግና አሰራር ማሻሻያዎችን እያደረገች መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የአሰራር ስርዓቶችን ከማሻሻል ባለፈ በአፍሪካ ደረጃ የጋራ ማዕቀፍ ግዢን ለመፈጸም የሚያስችል አቅም እንዳላት ገልፀዋል። የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለው ዓለም አቀፍ ተደራሽነት መድኃኒቶችን ለማከፋፈል ግዙፍ አቅም መሆኑን ጠቅሰው፥ ደረጃቸውን የጠበቁ የማቆያ ማዕከሎች መኖራቸውንም አንስተዋል። የአፍሪካ የበሽታ ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል የሀገር ውስጥ አምራቾች አስተባባሪ ዶክተር አበበ ገነቱ ውይይቱ በአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የሚተገበር የጋራ የመድሀኒትና ክትባቶች የማዕቀፍ ግዢን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል። የግዢ ማዕቀፉን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አንስተው የዛሬው መድረክም የሀገራትን ልምድ ለመቅሰም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። አህጉራዊ የግዢ ማዕቀፉን በ10 ሀገራት በመጀመር ወደሌሎች ለማስፋት መታቀዱንም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብድልቃድር ገልገሎ በአነስተኛ መጠን የሚፈለጉ መድሀኒቶች ግዢ ከዋጋና መጠን አንፃር ፈታኝ መሆኑን አንስተዋል። አህጉራዊ የጋራ የማዕቀፍ ግዢ ስርዓቱ ይህን ችግር ለመፍታት የሚረዳ መሆኑን ጠቁመው፥ በውይይቱ ላይ ኢትዮጵያ በመድሀኒት ግዢ ያላትን ልምድ እንደምታቀርብ ተናግረዋል።
ዘመናዊ የሲኒማ ኮምፕሌክሱ መንግሥት ለኪነጥበብ ማንሰራራት ያለውን ፅኑ አቋም ያረጋገጠበት ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Oct 14, 2025 41
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ዛሬ ተመርቆ ሥራ የጀመረው አዲስ የሲኒማ ኮምፕሌክስ መንግሥት ለኪነጥበብ ማንሰራራት ያለውን ፅኑ አቋም ያረጋገጠበት ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ24 ሺህ ካሬ ላይ ያስገነባውን አዲስ የሲኒማ ኮምፕሌክስ መርቆ ሥራ አስጀምሯል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ መንግሥት የኪነጥበብ ዘርፍ ለሀገር ግንባታ ያለውን አስተዋጽኦ በመገንዘብ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። ይህንንም ተከትሎ ከፍተኛ በጀት በመመደብ የዘርፉን ዕድገት የሚያረጋግጡ መሰረተ ልማቶችን እየገነባ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ለሲኒማ ኢንዱስትሪው ምቹ ግብዓቶች እንዲሟሉ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል። ይህም የሀገራችንን የሲኒማ ኢንዱስትሪ በዓለም አደባባይ ለማስጠራት እና እንዲተዋወቅ ያደርጋል ነው ያሉት። ዛሬ የተመረቀው አዲስ የሲኒማ ኮምፕሌክስ እጅግ ዘመናዊና ወቅቱ የደረሰበት ቴክኖሎጂ የተሟላለት መሆኑን ከንቲባዋ ተናግረዋል። ይህ ዘመናዊ ኮምፕሌክስ ለዘርፉ ቀጣይ እድገት አይተኬ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል። የዘመናዊ የሲኒማ ኮምፕሌክሱ መገንባት መንግሥት ለኪነጥበብ ማንሰራራት ያለውን ፅኑ አቋም ያረጋገጠበት ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በሲኒማ ኮምፕሌክሱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ የብልፅግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፣ የፌዴራልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
በሀዲያ ዞን የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የዘርፉን ስኬቶች ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Oct 14, 2025 33
ሆሳዕና፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ በሀዲያ ዞን የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል በዘርፉ እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ፡፡ የዞኑ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል፡፡ በመምሪያው የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ መሰረት አበራ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በዞኑ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡ ለእንስሳት ጤና የሚሆን መኖ ከማዘጋጀት ጀምሮ ዝርያቸውን ለማሻሻል የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በዘርፉ እየተከናወነ ባለው ዘመናዊ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል። የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ዮሐንስ በበኩላቸው በከተማው የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል ከወተት ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ባለፈው ዓመት በተከናወነው የእንስሳት ዝርያ የማሻሻል ስራን 82 በመቶ ላይ ማድረስ መቻሉን ጠቅሰው፤ በዚህም የወተት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በተከናወነው ስራ አበረታች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡ በሆሳዕና ከተማ በሊች አምባ ቀበሌ በእንስሳት እርባታ ላይ የተሰማሩት አቶ ዳንኤል ብርሃኑ እና በከተማው የሄጦ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ግርማ ቲርካሶ፤ መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ በሰጠው ትኩረት የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ትግበራው ውጤታማ እያደረገን ነው ብለዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና አርሶ አደሮች ተገኝተዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ የወጪ ንግድ አፈፃፀሙን ቀጣይነት እንዲኖረው አድርጓል
Oct 14, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የወጪ ንግድ አፈፃፀሙን ከፍተኛ ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት እንዲኖረው ማድረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ ተካሂዷል፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በሩብ ዓመቱ በዋና ዋና ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በሩብ ዓመቱ በወጪ ንግድ አፈጻጸም፣ በኦንላይን ንግድ ምዝገባ፣ በድህረ ፈቃድ ቁጥጥር፣ በዓለም የንግድ ድርጅት ድርድር እንዲሁም የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን በማስጀመር እመርታዊ ለውጥ ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት የወጪ ንግድን በዓይነት፣ በመጠንና በገቢ በማሳደግ፣ ዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር አስተማማኝ የገበያ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ግብ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል፡፡ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ክረምት እንደመሆኑ ለንግዱ ማህበረሰብ ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት አስቸጋሪ መሆኑን አንስተዋል። ይሁን እንጂ በበጀት ዘመኑ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከወጪ ንግድ ከ 2 ነጥብ 48 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል ብለዋል፡፡ የወጪ ንግድ አፈፃፀምን በተመለከተ በኩራት መናገር የሚቻልበት መሆኑን ገልጸው፤ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 65 በመቶ ብልጫ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ የተመዘገበው ውጤት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 980 ሚሊዬን ዶላር ብልጫ እንዳለው ጠቅሰው፤ በበጀት ዓመቱ የታቀደውን 9 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ማሳካት እንደሚቻል ያሳያል ብለዋል፡፡ ይሄውም የኢትዮጵያ የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የወጪ ንግድ አፈፃፀሙን ከፍተኛ ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ማድረጉን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከኦንላይን ንግድ ምዝገባ ከ980 ሺህ በላይ የንግድ ፈቃድ ምዝገባና ዕድሳት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ የኦንላይን ንግድ ምዝገባ 141 በመቶ አፈፃፀም መመዝገቡን በማንሳት፤ በበጀት ዓመቱ ማጠናቀቂያ የታቀደውን ሶስት ሚሊዬን ማሳካት እንደሚቻል ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነትን ለማሳካት 6ኛው የሥራ ላይ የቡድን ስብሰባ ያደረገችበት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ከስድስት ሀገራት ጋር ውጤታማ የሁለትዮሽ የገበያ ድርድር መደረጉን ተናግረዋል። ከሌሎች ሀገራት ጋርም ቀልጣፋ ድርድር እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው፤ ድርድሩ እንደሚሳካ ተስፋ ሰጭ ምልክቶች እየታዩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የብዙዎች ጥያቄ የነበረውን የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ትግበራ በአየርና በየብስ ትራንስፖርት መጀመር መቻሉን ተናግረዋል፡፡ አጠቃላይ ሩብ ዓመቱ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ተጠናክሮ የቀጠለበት መሆኑን ጠቁመው፤ አፈጻጸሙ በኢትዮጵያ ልክ ለመድረስ ከዚህ በላይ መስራት እንዳለብን አሳይቶናል ብለዋል፡፡
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የኢትዮጵያን የሪፎርም አጀንዳ መደገፉን እንደሚቀጥል ገለጸ
Oct 14, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) ለኢትዮጵያን የሪፎርም አጀንዳ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የኢትዮጵያ ልዑክ በዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(IMF) አመታዊ ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። በሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራው ልዑክ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ያካተተ ነው። የኢትዮጵያ ልዑክ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ናይጀል ክላርክ እና ከተቋሙ የአፍሪካ የስራ ክፍል ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ከኢትዮጵያ ሀገር በቀል ማክሮ ኢኮኖሚ አጀንዳ ጋር የተሳሰረው የአይኤምኤፍ ድጋፍ ፕሮግራም ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ለኢትዮጵያ የሪፎርም አጀንዳ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አድንቀዋል። ሪፎርሙ የኢትዮጵያን ሙሉ የኢኮኖሚ አቅም ለመጠቀም፣ የስራ ዕድል ለመፍጠርና የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የኑሮ ደረጃ ማሻሻልን ያለመ ነው ብለዋል። ሚኒስትሩ የሪፎርሙን ሂደት እና እስከ አሁን የተገኙ ውጤቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የዋጋ ንረት በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን፣ ወርቅን ጨምሮ የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ እድገት ማሳየቱን፣ የፊሲካል ምህዳሩን ያሰፋው የግብር ማሰባሰብ አቅም ማደግ እና የኢትዮጵያ የቢዝነስ ከባቢ ሁሉን አቀፍ መሻሻልን ለአብነት ጠቅሰዋል። አይኤምኤፍ ሪፎርሙ ካለው ግዝፈት አኳያ የሚያደርገውን የፋይናንስ ድጋፍ እንዲያሳድግም ጠይቀዋል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ለአይኤምኤፍ ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ መንግስት ቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ የዕዳ ሽግሽግ(G20 Common Framework debt treatment) ስር ከኢትዮጵያ ኦፊሴላዊ አበዳሪዎች ኮሚቴ እያደረገ ያለውን ድርድር ላይ የታዩ አዎንታዊ ለውጦችን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የዕዳ ሽግሽጉ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሪፎርም ፕሮግራም ወሳኝ ምሰሶ መሆኑን አመልክተው በፋይናንስ ዘርፉ ላይ እየተደረጉ ባሉ ሪፎርሞች የተገኙ ውጤቶችን አስመልክቶም ገለጻ አድርገዋል። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) በኢትዮጵያ እየታየ ያለውን ጠንካራ የኢኮኖሚ እድገት፣ እየተሻሻለ የመጣው የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትና ኢኮኖሚውን ለውጭ ዘርፍ ክፍት የማድረግ ጥረቶችን ጨምሮ የታዩ ለውጦችን አድንቋል። የአይኤምኤፍ ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ናይጀል ክላርክ የኢትዮጵያ ጠንካራ እና ድፍረት የተሞላበት የሪፎርም አጀንዳ ለሌሎች ሀገራት ምሳሌ እንደሆነ ገልጸው ተቋሙ የኢትዮጵያን የሪፎርም አጀንዳ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ የሪፎርም ትግበራ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑን በውል እንደሚረዱ ገልጸው ለዚህም ዓለም ባንክን ጨምሮ ከሌሎች የልማት ፕሮግራሞች ጋር በመተባበር ተጨማሪ ሀብት ማሰባሰብ እንደሚገባ አመልክተዋል። ክላርክ እ.አ.አ ዲሴምበር 2025 ላይ በኢትዮጵያ ጉብኝት ለማድረግ ማቀዳቸውም ተመላክቷል። ሁለቱ ወገኖች አይኤምኤፍ በአዲስ አበባ በቀጣይ የኢትዮጵያን ብድር ፕሮግራም አስመልክቶ በሚያካሂደው አራተኛ ግምገማ ላይ በቅርበት ለመስራትም ተስማማተዋል። ግምገማው የኢትዮጵያ ሪፎርም ሂደትን በመገምገምና የሁለቱን ወገኖች ትብብር የሚያጠናክሩ ቁልፍ መስኮችን በመለየት የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ ልማትና ዘላቂ እድገት መደገፍ ላይ ያተኮረ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው
Oct 14, 2025 48
ኮምቦልቻ ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ) ፡-በኮምቦልቻ ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው በተደረገላቸው ድጋፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑ ተገለጸ። በከተማ አስተዳደሩ በምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚዎች እየለማ ያለ ሰብል ዛሬ ተጎብኝቷል። ከተጠቃሚዎች መካከል ወይዘሮ አበባ ፍቃዱ በሰጡት አስተያየት፤ በፕሮግራሙ ታቅፈው በተመቻቸላቸው የገቢ ማስገኛ ስራ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህም አካባቢን በማስዋብና ንጽህናን ከመጠበቁ በተጓዳኝ የተሰማሩበት የጓሮ አትክልት ልማት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ አልፈው ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ላይ እንደሆኑ አስረድተዋል። ልማቱን ከጀመሩበት ካለፈው ዓመት የበጋው ወቅት ወዲህ ድንች፣ ሽንኩርትና ሌሎችንም አትክልቶችን በማልማት በሚያገኙት ገቢ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን ገልጸዋል። በክረምቱ ወራትም ስንዴን ማልማታቸውንና ሰብሉ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሌላው የፕሮግራሙ ተጠቃሚ አቶ ጀማል ሰይድ፤ በአካባቢያቸው ጥቅም ላይ ያልዋለ መሬት ተሰጥቷቸው በማልማት ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን በማሳደግ ተጠቃሚ እንደሆኑ ተናግረዋል። በከተማዋ በፕሮግራሙ የታቀፉ ከ3 ሺህ 490 በላይ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ መሰማራታቸውን የገለጹት ደግሞ የኮምቦልቻ ከተማ ምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ እታፈራሁ አሰግደው ናቸው። የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች በአካባቢ ጽዳት በመሳተፍ ከሚያገኙት ወርሃዊ ገቢ በተጨማሪ ብድር በማመቻቸት በግብርና፣ በግንባታና ሌሎች ልማቶች በመሰማራት ተጨማሪ ጥሪት እንዲያፈሩ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥም ከ2 ሺህ በላይ የሚሆኑት በከተማ ግብርና በመሳተፍ በዓመት እስከ ሶስት ጊዜ እያመረቱ በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ ትርፍ ምርታቸውን ለገበያ እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል። የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ወንድወሰን ልሳነወርቅ በበኩላቸው፤ በከተማው በፕሮግራሙ የታቀፉ ወገኖች ጥቅም ላይ ያልዋለ መሬት አልምተው እንዲጠቀሙ በማመቻቸት ውጤታማ መሆናቸውን አብራርተዋል። በጉብኝቱ ላይ አመራሮች፣ የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ የድሮን ቴክኖሎጂ ምርቶችን ማምረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 14, 2025 31
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ የድሮን ቴክኖሎጂ ምርቶችን ማምረቱን አጠናክሮ መቀጠሉን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በሀገር ውስጥ ማምረት የጀመራቸውን ድሮኖች ምርት በማስፋት የድሮን ቴክኖሎጂን በምርምር እና ሥርፀት ለማሳደግ እንዲሁም ተግባራዊ ተሞክሮን ለማዳበር የሚያግዘውን ትብብር ለመፍጠር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከኢፌዴሪ አየር ኃይል፣ ከመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንደስትሪ ግሩፕ፣ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈራረሙን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ ገልጸዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ በመርሐ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት፥ ብሔራዊ ጥቅምን ከማስከበር እንዲሁም ካለው የላቀ ኢኮኖሚያዊና ስትራቴጂያዊ ፋይዳ አንጻር የድሮን ቴክኖሎጂን በራስ አቅም ማልማት ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ ነው፡፡ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባትም የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ተመርቆ ስራ የጀመረው ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ ለደኅንነት፣ ለመረጃ ስምሪት፣ለሲቪልና ለወታደራዊ አገልግሎቶች የሚውሉ ድሮኖች ምርትን አጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። የድሮን ቴክኖሎጂ በፈጣን ዕድገት ላይ የሚገኝ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሲሳይ፤ እንደ ሀገር ብሔራዊ ጥቅምን ከማስጠበቅ፣ ኢኮኖሚያዊ እድገትን ከማሳለጥ እንዲሁም ወደፊት የሚቃጡ ጥቃቶችን ውጤት ከመወሰን አንፃር ያለውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ በመመዘን በድሮን ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ ገልጿል፡፡ በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆንና በሀገር ውስጥ የተፈጠረውን የድሮን ቴክኖሎጂ ዐቅም ለማጎልበት የአንድ ተቋም እንቅስቃሴ ብቻ በቂ ባለመሆኑ ከአምስቱ ተቋማት ጋር በትብበር እና አጋርነት ለመስራት ስምምነቱ ማስፈለጉን የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ አብራርተዋል፡፡ ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ የሚያመርታቸውን ድሮኖች በዓይነትና በጥራት ለማሳደግ የድሮን ቴክኖሎጂ የሚጠቀማቸውን ስማርት ሴንሰሮች በተመለከተ ከአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አስተዳደር፤ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዘርፉን ምርምር ውጤቶችና የሰለጠነ የሰው ኃይል፤ በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንደስትሪ በኩል ለውጊያ የሚውሉ ድሮኖች የሚታጠቋቸው ጦር መሳሪያዎች ምርትን፤ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የካበተ የአቪዬሽን ዘርፍ ተሞክሮ እንዲሁም ከኢፌዴሪ አየር ኃይል በኩል ተግባራዊ ልምምድ ለመቅሰም ታልሞ የትብበር ስምምነቱ መፈረሙ ተመልክቷል፡፡ ከመግባቢያ ሰነድ ፊርማው በኋላ የስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪና የድሮን ምርቶቹ የተጎበኙ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በዘርፉ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማረጋገጥ እና በሀገር ውስጥ ያሉትን የተለያዩ ተቋማት እና ዩኒቨርሲቲዎች ዕውቀት፣ ልምድና ሀብት በመደመር ውጤታማነትን ለማረጋገጥ በትብብር ለመስራት የወሰደው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘርፉ በሚያደርጋቸው ምርምር እና ልማት እንዲሁም የሰው ኃይልን በማሰልጠን ከስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ ያለውን ተሞክሮ ማካፈል ብቻ ሳይሆን ወደፊት በስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ የሚመረቱ ድሮኖችን መጠቀም የሚችልበት ዕድሎች መኖራቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በዓለማችን ሀገራት ውጥረት ውስጥ በገቡ ጊዜ ሉዓላዊነታቸውን ለማስከበር በሚያካሄዷቸው ማናቸውም ኦፕሬሽኖች ላይ የድሮን ቴክኖሎጂ ሚናው እያደገ መምጣቱን የጠቀሱት የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንደስትሪ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታቸው ሃይለማርያም፤ የሀገራችንን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዘርፉን በራስ አቅም በተገቢው መንገድ ለመጠቀም በትብብር ለመስራት አጋጣሚው ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ አነስተኛ እና መካከለኛ ድሮኖችን በማምረት ስራውን የጀመረ ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ እ.አ.አ በ2030 ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸው ትላልቅ ድሮኖችን በማምረት ለዓለም ገበያ የማቅረብ ራዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደምም ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ስምምነት ፈጽሟል።
በኢትዮጵያ ቁልፍ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ላይ የሚቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም ተገንብቷል
Oct 14, 2025 114
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ቁልፍ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ላይ የሚቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባቱን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ገለጹ፡፡ የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ተቀርፆ ተግባራዊ ተደረጓል። ስትራቴጂው ዲጂታላይዜሽን፣ ዘመናዊ አገልግሎት አሰጣጥ አና ቴክኖሎጂን ማዕከል ያደረገ በመሆኑ በሁሉም መስኮች ገቢራዊ እንዲሆን በትኩረት መሰራቱን ገልጸዋል፡፡ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ዜጎች በቴክኖሎጂ ላይ ያላቸውን አረዳድ በማሳደግ ለዲጂታል መስፋፋት ዕድል ፈጥሯል ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ ከቴክኖሎጂ መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሳይበር ጥቃት ይዘቱንና አይነቱን እየቀያየረ እየተከሰተ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ በዚህም የሳይበር ጥቃትን ቀድሞ መከላከል የሚያስችል አቅም መገንባት በሚያስችል የወትሮ ዝግጁነት የአሰራር ሥርዓት የቁጥጥርና ምላሽ መስጫ ማዕከላትን በማቋቋም ሁልጊዜም በተጠንቀቅ እየሰራን ነው ብለዋል፡፡ ማዕከላቱን በቴክኖሎጂና በብቁ የሰው ኃይል በማሟላት የቅድመ መከላከልና ዓለም አቀፍ የቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ አስተዳደሩ በጥናት የተደገፈ የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት፣ ፖሊሲና ስትራቴጂ በመቅረጽ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት ዘርግቷል ብለዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ዘመኑን የዋጀ አዲስ የሳይበር ደህንነት ፖሊሲ መጽደቁን ገልጸው፤ ፖሊሲው ዲጂታላይዜሽንን ከማስረጽ ባሻገር የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በታዳጊዎች የሰመር ካምፕ የሳይበር ታለንት ማዕከል የሚሰጠው ትምህርት፣ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር የሚሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች የዜጎችን ግንዛቤ በማሳደግ ገንቢ ሚና እየተወጡ እንደሚገኙም ገልጸዋል፡፡
በስፔስ ሳይንስ ዘርፍ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች ለማብቃት በተከናወኑት ስራዎች ውጤቶች ተገኝተዋል
Oct 14, 2025 157
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡- በስፔስ ሳይንስ ዘርፍ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች ለማብቃት በተከናወኑ ስራዎች ውጤቶች መገኘታቸውን የስፔስ ሳይንስና የጂኦስፓሻል ኢንሲቲትዩት ገለጸ። የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ቤቴልሄም ንጉሴ ለኢዜአ እንደገለጹት ተቋሙ ባለፉት አምስት ዓመታት በስፔስ ሳይንስ ዘርፍ ብቁ የሆኑና በቀጣይ ቴክኖሎጂው ላይ ውጤታማ ሥራ የሚሰሩ ታዳጊዎችን ለማፍራት ሲሰራ ቆይቷል። በዘርፉ ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊዎች ለአራት ዓመታት ስልጠና ከወሰዱ በኋላ በስልጠናው ማጠናቀቂያ የራሳቸውን ፕሮጀክት እንዲሰሩና ስታርት አፕ እንዲጀምሩ ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ ገልጸዋል። ይህ ሂደት ታዳጊዎቹ በዓለም አቀፍ ስልጠናዎችና ውድድሮች የመሳተፍ እድል እንዲያገኙ በማድረግ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ባለ ልዩ ተሰጥኦዎችን ማፍራት አስችሏል ብለዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ታዳጊዎቹ በፍላጎታቸው መሠረት በምርምር፣ በስታርት አፕ፣ ነፃ የትምህርት እድልና ሌሎች ዕድሎችን አግኝተው የዘርፉ ተረካቢ እንዲሆኑ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የኢትዮ ስፔስ ኤንድ ስፓሻል ኪድስ ክለብ አስተባባሪ ኢንጂነር አልአዛር ስዩም በበኩላቸው፣ ዓለም አቀፍ ስኬት ላይ የደረሱ ሰዎች ተሰጥኦዋቸውን በሚገባ በሚደግፍ ሥርዓት አማካይነት ስኬታማ መሆን መቻላቸውን ጠቅሰው፣ ይህንኑ ተሞክሮ በሀገር ውስጥ የመተግበርን አስፈላጊነት አጽንኦት ሰጥተዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት 411 ተማሪዎች ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቅሰው፣ በክልሎች የስልጠናውን ተደራሽነት ለማሳደግ ከ2 ሺህ በላይ የሚሆኑ ታዳጊዎች በኦንላይን ስልጠና መጀመራቸውን ጨምረው ገልጸዋል። ኢንጂነር አልዓዛር ስልጠና ያጠናቀቁ ተማሪዎች ፕሮጀክታቸውን በስታርት አፕ ወደ ምርት ወይም አገልግሎት እንዲቀይሩት በተመራማሪዎች እንደሚደገፉ ጠቁመዋል። ለአብነትም፣ የድሮን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ህንፃዎች ላይ ለጽዳትና ለእሳት ማጥፊያ አገልግሎት የሚውል ቴክኖሎጂ ወደ ሥራ ለማስገባት ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡን ሰልጣኞች መካከል የ18 ዓመቷ ሐና ጌቱ እና የ17 ዓመቱ ቶማስ በላይ፣ ስልጠናው ችግር ፈቺ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን ለመፍጠር እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል። ታዳጊዎች በቀጣይ የራሳቸውን ድርጅት ለማቋቋም እና ወቅቱ የሚፈልገውን በቴክኖሎጂ የታገዘ ምርት ለመስራት ማቀዳቸውን ገልጸዋል።
በደሴ ከተማ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው
Oct 14, 2025 57
ደሴ ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ በተያዘው ወር የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። በደሴ ከተማ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የዲጂታል አሰራርን ለማስፋት እየተደረገ ያለውን ጥረት በተመለከተ ኢዜአ የከተማ አስተዳደሩን ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝን አነጋግሯል። ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው በማብራሪያቸውም በከተማ አስተዳደሩ የህዝብን አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተጠያቂነት ያለበት ለማድረግ የተቀናጀ ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑን አንስተዋል። በተለይም የአገልግሎት እንግልትን ለማስቀረትና በአንድ ስፍራ ላይ በርከት ያሉ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችል የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። አገልግሎቱን በተያዘው ወር አጋማሽ ላይ ለመጀመርም የግንባታ ማስተካከያ፣ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ዝግጁ የማድረግ፣ የአገልግሎት መስጫ ግብዓቶችን የማሟላትና ብቁ የሰው ሃይል ዝግጁ እየተደረገ ነው ብለዋል። በማእከሉ በተለይም የመሬት ነክ፣ ገቢዎች፣ ንግድ፣ የቴሌኮም አገልግሎት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የባንክ፣ የኢሜግሬሽንና ሌሎችም አገልግሎቶች ተጀምረው እየሰፋ የሚሄድ ይሆናል ብለዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቃሲም አበራ፤ የሕብረተሰቡን የልማትና የአገልግሎት ፍላጎቶች መሰረት ያደረጉ ተግባራት በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ የተቀላጠፈ ለማድረግ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት አገልግሎቱን ለማስጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ተናግረዋል። በከተማው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሲጀመር ለጊዜው በ39 የአገልግሎት አይነቶች ስራ የሚጀመር መሆኑን አንስተው አገልግሎቱ እየበዛና እየሰፋ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በቡርኪናፋሶ አቻው ተሸነፈ
Oct 13, 2025 174
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ከቡርኪናፋሶ ጋር ባደረገው ጨዋታ 3 ለ 1 ተሸንፏል። ማምሻውን በኦገስት 4 ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ተቀይሮ የገባው ፒዬር ላንዲ ካቦሬ በ64ኛው፣ በ82ኛው እና በ96 ደቂቃ የማሸነፊያ ግቦቹን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። ቢኒያም አይተን በ84ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ በምድብ አንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ በዘጠኝ ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ቡርኪናፋሶ በ21 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ምርጥ ሁለተኛ ሆኖ በጥሎ ለማለፍ ከሚሳተፉ አራት የአፍሪካ ሀገራት አንዷ የመሆን እድሏን አስፍታለች። በዚሁ ምድብ ማምሻውን በተደረገው ጨዋታ ግብጽ ጊኒ ቢሳውን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ለዓለም ዋንጫ ያለፈው ቡድኑ በ26 ነጥብ ምድቡን በመሪነት አጠናቋል። በዚሁ ምድብ በተደረገው ጨዋታ ሴራሊዮን ጅቡቲን 2 ለ 1 አሸንፋለች።
ኢትዮጵያ የዓለም ዋንጫ የመጨረሻ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዋን ከቡርኪናፋሶ ጋር ዛሬ ታደርጋለች
Oct 12, 2025 145
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ዛሬ ከቡርኪናፋሶ ጋር ትጫወታለች። የሀገራቱ ጨዋታ በኦገስት 4 ስታዲየም ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ይደረጋል። በምድብ አንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ በዘጠኝ ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በፊት ከጊኒ ቢሳው ጋር ባደረገው የማጣሪያ መርሃ ግብር 1 ለ 0 በማሸነፍ በምድቡ ሁለተኛ ድሉን ማስመዝገቡ ይታወቃል። በብራማ ትራኦሬ የሚሰለጥነው የቡርኪናፋሶ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በፊት ከሴራሊዮን ጋር ባደረገው ጨዋታ 1 ለ 0 አሸንፏል። ቡድኑ ነጥቡን ወደ 18 ከፍ በማድረግ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሁለቱ ሀገራት በዚሁ ምድብ ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ ቡርኪናፋሶ 3 ለ 0 ማሸነፏ የሚታወስ ነው። ሀገራቱ ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው አምስት የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ አንድ ጊዜ ስታሸንፍ ቡርኪናፋሶ ሶስት ጊዜ ድል ቀንቷታል። አንድ ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። በጨዋታዎቹ ቡርኪናፋሶ 12 ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ኢትዮጵያ ሶስት ግቦችን አስቆጥራለች። ከዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ ለሆነው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የዛሬው ጨዋታ የማጣሪያ ጉዞውን በድል ለመደምደም ያስችለዋል። ቡርኪናፋሶ ማሸነፍ ከቻለች ለዓለም ዋንጫው ለማለፍ በሚደረገው የጥሎ ማለፍ ውድድር ለመሳተፍ የሚያስችላትን እድል ታሰፋለች። በዚሁ ምድብ የምትገኘው ግብጽ በ23 ነጥብ ለዓለም ዋንጫ በቀጥታ ማለፏ የሚታወስ ነው። በምድብ አንድ ግብጽ ከጊኒ ቢሳው፣ ጅቡቲ ከሴራሊዮን ዛሬ በተመሳሳይ ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በድሬዳዋ ከተማ ሊደረጉ የነበሩ የሊጉ የመክፈቻ ጨዋታዎች ወደ ሃዋሳ ተዘዋውረዋል
Oct 11, 2025 195
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በድሬዳዋ ሊደረጉ የነበሩ የመክፈቻ ጨዋታዎች ወደ ሃዋሳ መዘዋወራቸውን የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታወቀ። የሊጉ የመጀመሪያ ዘጠኝ ሳምንታት ውድድር በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ እንደሚደረግ መገለጹ ይታወቃል። ይሁንና በአሁኑ ወቅት ድሬዳዋ ከተማ ውድድሩን ለማስተናገድ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠ በመሆኑና ዝግጁ አለመሆኑን በመግለጹ ድሬዳዋ ላይ ሊደረጉ የነበሩ የመክፈቻ ሳምንታት ጨዋታዎች ወደ ሃዋሳ ከተማ መዞሩን ማህበሩ ገልጿል። የተስተካከለውን መርሃ ግብር በቅርቡ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል። 20 ክለቦች በሁለት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች ነው
Oct 13, 2025 146
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ገለጹ፡፡ በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስተባባሪነት በአረንጓዴ ትራንስፖርትና በታዳሽ ኃይል ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች የአዳማ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተጎብኝቷል፡፡ በጉብኝቱ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን፣ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰንን ጨምሮ ከኢትዮጵያ እና ኬንያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ ኩባንያዎች ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴዔታ በርኦ ሀሰን በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የትራንስፖርት ዘርፉን ጨምሮ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ ባከናወነቻቸው ተግባራት በርካታ ለውጦችን አስመዝግባለች ብለዋል፡፡ ለዚህም በሕዳሴ ግድብ፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብርና በንፋስ ኃይል ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች ትልቅ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዘርፉን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅና ከአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የጸዳ እንዲሆን ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል፡፡ መንግሥት ታዳሽ ኃይል የሚጠቀም የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍን እውን ለማድረግ ጠንካራ የፖሊሲ ድጋፍ ስለማድረጉ አንስተዋል። በዚህም በርካታ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በማንሳት፥ ባለሀብቶችም በዘርፉ ኢንቨስት እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና መንግስት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓት የተሰማሩ ተቋማትን እንደሚያበረታታ አረጋግጠዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለዓለም ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ናቸው ብለዋል፡፡ በተለይ ደግሞ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ የወሰደው እርምጃ ይበል የሚባል ነው ብለዋል፡፡ ሀገራቸው ይህንን ተግባር እንደምትደግፍም አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ሳምንት ከነገ ጥቅምት 4 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 6 ቀን 2018 በአዲስ አበባ ይካሔዳል፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ የብዙሃን ትራንፖርት፣ ባቡር፣ ኮሪደር ልማት፣ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች እንዲሁም በፖሊሲ ረገድ እያከናወነች ያለችውን ተጨባጭ ሥራ እንደምታቀርብም ተገልጿል።
ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ተረፈ ምርቶችን ወደ ሐብት በመቀየር ውጤታማ እየሆኑ ነው
Oct 13, 2025 90
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ተረፈ ምርቶችን ወደ ሐብት በመቀየር ገቢ ከማመንጨት ባለፈ በአካባቢ ጥበቃ እና በስራ ዕድል ፈጠራ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ገለጹ። በኢትዮጵያ በቅርቡ ብሔራዊ የሰርኩላር ኢኮኖሚ ፍኖተ ካርታ ይፋ የተደረገ ሲሆን ቆሻሻን መልሶ መጠቀምን ማስፋፋት፣ ለአካባቢ ተስማሚ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት እና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ላይ የተመሠረቱ የሥራ ዕድሎችን ማስፋት ከዋና ዓላማዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የአካበቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ እንደተናገሩት ለፍኖተ ካርታው ውጤታማነት የግል ዘርፉ ተሳትፎ የጎላ ነው። ፍኖተ ካርታው ጽዱ ኢትዮጵያን ከማሳካት አንጻር የግሉ ዘርፍ ትልቁን ድርሻ እንዲወጣ የሚያስችል ነው ብለዋል። የግሉ ዘርፍ የሚያስፈልገውን የፋይናንስ፣ የቴክኖሎጂና ሌሎች ድጋፎች ያካተተ የተቀናጀ ስርዓት የሚዘረጋ መሆኑንም ተናግረዋል። ብሔራዊ የሰርኩላር ኢኮኖሚ ፍኖተ ካርታ ግቦችን ከማሳካት አንጻር ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ተረፈ ምርቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ለአካባቢ ተስማሚና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ምርቶችን በማምረት የጀመሩት ሥራ ምሳሌ ሆኖ የሚቀርብ ነው። ወጣት ሚካኤል ኃይሌ ጥቅም ላይ የዋሉ ወረቀቶችን በመሰብሰብና መልሶ በመጠቀም የተለያዩ ምርቶችን በማምረት ላይ እንደሚገኝ ይናገራል። ምርቶቹም ለተቋማት ማስታወቂያ፣ ለጌጣጌጥ፣ ለስጦታና ለሌሎች አገልግሎቶች እየዋሉ መሆኑን ጠቁሞ የቆሻሻ አሰባሰብ ሂደቱን ከማህበረሰቡ ጋር በማስተሳሰር የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልጿል፡፡ ከየተቋማቱ የሚጣሉ ወረቀቶችን ለሚሰበስቡ ለበርካታ የጽዳት ሠራተኞችና ሴቶች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸውም አስረድቷል። ወጣት ኢያሱ መዝገቡ የሙዝ ልጣጭን ከሌሎች ግብዓቶች ጋር በመጠቀም ለቤትና ቢሮ ቁሳቁሶች፣ ለጫማ እንዲሁም ለተለያዩ የቆዳ ምርቶች የሚውል አካባቢን የማይጎዳ ቀለም እያመረተ መሆኑን ገልፅዋል። የእንጨት ተረፈ ምርቶችን በመጠቀም በውስጡ የሚገኘውን መርዛማ ጋዝ በማውጣት ለጤና የማይጎዳ የከሰል ምርት እያመረተ እንደሚገኝ የተናገረው ደግሞ ወጣት ኢዮብ አለሙ ነው፡፡ ምርቱ ከእንጨት ተረፈ ምርት የሚመረት በመሆኑ የደን ጭፍጨፋን በመከላከል ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጿል። ይህም የሀገሪቱን የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር እና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሥራዎችን በመደገፍ ረገድ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት አመልክቷል። ወጣቶቹ እንዳሉትም በቀጣይም ምርቶቻቸውን በስፋት በማምረት የሥራ ዕድል ፈጠራን ይበልጥ ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ገልጸዋል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን በክረምት ወራት ለተተከሉ ችግኞች የሚደረገው እንክብካቤ ቀጥሏል
Oct 11, 2025 201
ጊምቢ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን በክረምት ወራት ለተተከሉ ችግኞች የሚደረገው እንክብካቤ መቀጠሉን የዞኑ የግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። የምዕራብ ወለጋ ዞን የግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፈይሳ ሀምቢሳ እንደገለጹት በዞኑ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተተክለዋል። ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች ውጤታማ እንዲሆኑ በዞኑ ነዋሪዎች የችግኝ እንክብካቤ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ወቅትም በተለይም ባለፈው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በተጠናከረ መልኩ እየተካሄደ ነው ብለዋል። በአጠቃላይ በዞኑ ባለፉት ዓመታት በተከናወነ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች አካባቢውን አረንጓዴ ከማልበስ ባለፈ ለግብርና ስራም እገዛ እያደረጉ መሆኑ ገልጸዋል። በችግኝ እንክብካቤው እየተሳተፉ ከሚገኙ መካከል ወይዘሮ ለሊሴ ብርሃኑ፣ በክረምት ወራት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን እየተንከባከቡ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በአካባቢያቸው በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተተከሉ ችግኞች ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ መሆኑን በመገንዘባቸው አሁንም በእንክብካቤው መጠንከራቸውን ጠቅሰዋል። አቶ ገረመው ነገራ በበኩላቸው የተተከሉ ችግኞች ለውጤት እንዲበቁ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ሁሉም በየአካባቢው ችግኞችን በመንከባከብ ለውጤት ማብቃት አለበት ያሉት ደግሞ አቶ ነጻነት አበበ ሲሆኑ ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች የተለያየ ጥቅም እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያሏትን ተሞክሮዎች የምታቀርብበት አህጉራዊ ሁነት
Oct 10, 2025 284
አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ “ አፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ዊክ 2025” የተሰኘ የአፍሪካ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ሳምንት ከጥቅምት 4 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል። ሳምንቱ “ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የትራንስፖርት ስርዓትን ማረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ይካሄዳል። ተቀማጭነቱን ኬንያ ናይሮቢ ያደረገው ”አፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ አሊያንስ” የተሰኘ ድርጅት፣ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር፣ የተባበሩት መንግስታት የአካባቢ ጥበቃ ፕሮግራም እና ሌሎች አጋሮች ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተዋል። በሁነቱ ላይ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ኢኖቬተሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የትራንስፖርት ዘርፍ መሪ ተዋናያን ይሳተፋበታል። ሳምንቱ አፍሪካ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽርካሪዎች የምታደርገውን ሽግግር ማፋጠን ዋንኛ ትኩረቱ አድርጓል። የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን በአረንጓዴ ትራንስፖርት ሳምንቱ ላይ ከ500 በላይ ሰዎች በአካል እና ከ2000 በላይ ሰዎች በበይነ መረብ አማራጭ እንደሚሳተፉ ለኢዜአ ገልጸዋል። በሳምንቱ ላይ ከ30 በላይ የውይይት መድረኮች እና አውደ ርዕዮች እንደሚካሄዱ ጠቅሰው ከነዚህም አንዱ የአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት የሚገኙበት መድረክ እንደሆነ ተናግረዋል። አረንጓዴ ትራንስፖርትን የተመለከቱ የጥናት ውጤቶች እና ግኝቶች ይፋ እንደሚደረጉም ነው የገለጹት። ከሁነቶቹ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪ ጉብኝት መርሃ ግብር እንደሚኖር ጠቅሰው ከ200 በላይ ተሳታፊዎች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ገጣጣሚዎችን፣ የኤሌክትሪክ ባሶች እንቅስቃሴ፣ የተሰሩ የኃይል መሙያ ማዕከላት፣ ዴፖዎች እንዲሁም በሽያጭ፣ አቅርቦት እና ጥገና የተሰማሩ አካላትን እንቅስቃሴ እንደሚጎበኙ አመልክተዋል። በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተካሄደው “ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2024” ዓለም አቀፍ አውደ ርዕይና ሲምፖዚየም ላይ የተነሱ አጀንዳዎች አፈጻጸም እንደሚገመገምም እንዲሁ። የትራንስፖርት ሳምንቱ አካል የሆነ የ1 ሺህ 600 ኪሎ ሜትር የኤሌክትሪክ መኪና ጉዞ በመካሄድ ላይ መሆኑን ጠቅሰው ተጓዦቹ ዛሬ ሶስተኛ ቀናቸውን እንደያዙና የፊታችን እሁድ አዳማ እንደሚደርሱ ጠቁመዋል። ጉዞው በኤሌክትሪክ መኪናዎች አማካኝነት ቀጣናዊ የትራንስፖርት ስርዓትን መፍጠርን ያለመ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ በማድረግ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን የማስፋት ስራ እያከናወነች እንደምትገኝም ነው ሚኒስትር ዴኤታው የገለጹት። በኢትዮጵያ መንገዶች ላይ ካሉ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ተሽከርካሪዎች መካከል ከ115 ሺህ በላይ የኤሌክትሪክ መኪኖች እንደሚገኙበት ጠቁመው ይህም ከአጠቃላይ ተሽከርካሪዎች የሰባት መቶ ድርሻ እንደያዙ ጠቁመዋል። የግሉን ዘርፍ እና የተለያዩ አካላትን በማሳተፍ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የተሽከርካሪዎች ኃይል መሙያ ጣቢያዎች መገንባታቸውን ነው ያብራሩት። በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት 16 ተቋማት የኤሌክትሪክ መኪናዎችን እየገጣጠሙ መሆናቸውን ጠቅሰው የአረንጓዴ ትራንስፖርት በህዝብ ትራንስፖርት ላይ እየሰፋ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ አውቶቢሶች የማስፋት ስራ ውጤት እያስገኘ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው መንግስት በኤሌክትሪክ መኪና ለተሰማሩ አካላት የታክስ ማበረታቻ ማድረጉንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት በፖሊሲ እና ስትራቴጂ በመደገፍ ውጤታማ ስራን እያከናወነች እንደምትገኝና ይህንንም መልካም ተሞክሮዋን በአህጉራዊው ሁነት ላይ እንደምታቀርብ አመልክተዋል። የትራንስፖርት ሳምንቱ አካል የሆነ የወጣቶች ጉባኤ በበይነ መረብ መካሄዱንና በዚህም መደረክ ላይ ኢትዮጵያ ያላትን ተሞክሮ ለአፍሪካ ሀገራት ማቅረቧን ገልጸዋል። የአፍሪካ አረንጓዴ ትራንስፖርት ሳምንት አህጉሪቷ ከብክለት የጸዳ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓት ለመፍጠር ለምታደርገው ጥረት አቅም የሚፈጥር መሆኑ ተመላክቷል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በሙሉ አቅም መተግበር ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው - መሐመድ አሊ ዩሱፍ
Oct 10, 2025 290
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ሙሉ ለሙሉ ገቢራዊ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 24ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሁነቶች በአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት እና ተወዳዳሪነት ተጽእኖ እያሳደሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከመቼው ጊዜ በላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሙሉ ለሙሉ በአፋጣኝ መተግበር እንደሚገባው የሚያመላክት ነው ብለዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ከቀረጥ ጋር ያልተያያዙ የንግድ ገደቦችን በማንሳት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተሳለጠ የንግድ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችሉ ማዕቀፎችን በመተግበር ለአጀንዳ 2063 መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኮሜሳ፣ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (ሳዴቅ) እና የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ (ኢኤሲ) የሶስትዮሽ ትብብር ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ማዕቀፉ የትስስር አጀንዳ ተምሳሌት እና አንድ የሆነች፣ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች አህጉር ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ የተስፋ ብርሃን ፈንጣቂ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር ቀጣናዊና አህጉራዊ የትስስር አጀንዳዎችን ትግበራ ለማፋጠን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንደሚያጠናክሩ ገለጹ
Oct 10, 2025 270
አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን የቆየ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። ጀርመን ለኢጋድ ቀጣና የተለያዩ የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፎችንም ይፋ አድርጋለች። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በልማት ትብብራቸው ዙሪያ በጅቡቲ ስትራቴጂካዊ ምክክር አድርገዋል። በምክክሩ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር እና ልማት ሚኒስቴር የምስራቅ አፍሪካ ዘርፍ ኃላፊ ሃኒንግ እና በጅቡቲ የጀርመን አምባሳደር ሄይከ ፉለር (ዶ/ር) ተገኝተዋል። ስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ የግንኙነት ማዕቀፎች ላይም መክረዋል። ፍልሰት እና አየር ንብረት ለውጥ የውይይቱ አበይት ማጠንጠኛዎች ናቸው። ሁለቱ ወገኖች የጀርመን ቀጣናዊ የፍልሰት ፈንድ ዳግም ማዋቀር ሂደት መልካም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በማንሳት የኢጋድ የቀጣናዊ የፍልሰት ፖሊሲ ማዕቀፍ ፣ የነጻ እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፎች እና የዜጎችን የአኗኗር ሁኔታ የማጠናከር ስራ ለመደገፍ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ጀርመን ለኢጋድ የፍልሰት ፖሊሲ ትግበራ ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ ትግበራ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ ቃል መግባቷን ኢዜአ ከቀጣናዊ ተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም ጀርመን በኢጋድ አባል ሀገራት ለሚከናወኑ የማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ስራዎች በቀጣናዊ የአደጋ ፋይናንስ ፕሮግራም አማካኝነት 22 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ መዘጋጀቷ ተመላክቷል። የፋይናንስ ማዕቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ድንገተኛ አደጋዎችን የመከላከል ስራዎች የሚደገፍ እና የኢጋድ የድርቅ አደጋን የመቋቋም እና ዘላቂነት ኢኒሼቲቭ ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን የሚደግፍ ነው። በስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች ውጤት ተኮር፣ አሳታፊ እና ተጠያቂነትን መሰረት ያደረገ አጋርነትን መፍጠር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢጋድ እና ጀርመን ትብብራቸውን ለማጠናከር፣ የጋራ ስራዎቻቸው የአባል ሀገራት የቅድሚያ ትኩረቶች ያማከሉ እንዲሆኑና የፖሊሲ ምክክራቸውን በመደበኛነት ለማከናወን ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ኢጋድ እና ጀርመን 37 ዓመታትን ያስቆጠረ አጋርነት እንዳላቸው መረጃዎች ያመለክታሉ።
የአፍሪካ ህብረት የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 7, 2025 337
አዲስ አበባ፤ መስከረም 27/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷ ወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን አስታወቀ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት ከፍተኛ አመራሮች ከሆኑት ዲያላ ሞሙኒ እና አህመድ ቤኒንግ ጋር በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል። የአፍሪካ ህብረት የወጣቶች ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ሊቀ መንበር ኡቺዚ ምካንዳዋየር በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል። የአፍሪካ ህብረት ስምምነቱ የአህጉሪቷ ወጣቶች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና ወጣቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። በስምምነቱ አማካኝነት የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት በሀገራት ደረጃ ያሉ የወጣት ምክር ቤቶች የሚያቀናጅ አህጉራዊ ማዕቀፍ እና ለአፍሪካ ወጣቶች እንደ ጋራ ድምጽ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ንቅናቄ የወለደው አህጉራዊ አደረጃጀት ሲሆን እ.አ.አ በ1962 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በጊኒ ኮናክሪ ባደረጉት ስብስባ ህብረቱን አቋቁመዋል። ህብረቱ የተመሰረተው በወቅቱ ወጣቶች አፍሪካ ከቅኝ ግዛት እንድትላቀቅ ለነበረው ትግል አቅም እንዲሆኑ ከማሰብ የመነጨ ነው። የወጣቶች ህብረቱ እንቅስቃሴ የፖለቲካ ድጋፍን በማሰባሰብ እና የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዲወጡ በማድረግ ረገድ ስትራጂካዊ ሚናውን ተጫውቷል። የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት እ.አ.አ በ2006 ባደረገው ስብስባ የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በድጋሚ የማደራጀት የውሳኔ ሀሳብ በማፅደቅ ህብረቱ የአህጉሪቷ የወጣት መዋቅር እንዲሆን በይኗል።
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አፍሪካ በዓለም መድረክ ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት ድጋፉን ሊሰጥ ይገባል- አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Sep 24, 2025 913
አዲስ አበባ፤ መስከረም 14/2018(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አፍሪካ በዓለም መድረክ ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት እያደረገችው ላለው ጥረት ድጋፍ እንዲሰጥ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጥሪ አቀረቡ። 80ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ከጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም አንስቶ በድርጅቱ ዋና መቀመጫ ኒውዮርክ እየተካሄደ ይገኛል። የጠቅላላ ጉባኤው አካል የሆነ ከፍተኛ የምክክር እና ክርክር መድረክ ዛሬ በኒው ዮርክ ተጀምሯል። “'ደህናነት በአብሮነት፤ 80 ዓመታት እና ከዚያ በላይ ለሰላም፣ ለልማት እና ለሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ” በሚል መሪ ሀሳብ ነው ጉባኤው የሚካሄደው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ “እየተለወጠ ባለው የዓለም የፖለቲካ ስርዓት ውስጥ የአፍሪካ ምልከታዎች” በሚል መሪ ሀሳብ ለጉባኤው ተሳታፊዎች የቪዲዮ መልዕክት አስተላልፈዋል። አምባሳደር ሳልማ በመልዕክታቸው አፍሪካ በተለያዩ መስኮች ራሷን ለመቻል እያከናወነቻቸው ያሉ ስራዎች ፍሬ እያፈሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች በራሷ ፋይናንስ በማድረግ ረገድ ለውጥ ማምጣቷን በማሳያነት ጠቅሰው የአፍሪካ የሰላም እና ደህንነት ማዕቀፍ በአፍሪካውያን ገንዘብ እና ባለቤትነት እየተመራ እንደሚገኝም አመልክተዋል። የአፍሪካ ህብረት የሰላም ፈንድ በአፍሪካውያን በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በትግበራ ላይ መሆኑን አንስተዋል። አምባሳደሯ በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ላይ ያላቸውን ሀሳብ ያጋሩ ሲሆን የንግድ ቀጣናው ዜጎች እና ገበያን ከማስተሳሰር ባለፈ ሰው ሰራሽ ድንበሮች በእኛ ላይ ከመጫናቸው በፊት የነበረውን የንግድ ትስስር እና ትብብር እንደሚመለስ ተናግረዋል። አፍሪካ በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረክ ያላት ድርሻ እያደገ መምጣቱን ገልጸው አህጉሪቷ በቡድን 20 ቋሚ መቀመጫ ማግኘቷ አበይት ማሳያ ነው ብለዋል። አፍሪካ በቡድን 20 ውስጥ ያገኘችው ቋሚ መቀመጫ ለዓለም ችግሮች መፍትሄ ያላትን አይተኬ ሚና በግልጽ የሚያመላክት እንደሆነም ተናግረዋል። እየተለወጠ ያለው የዓለም ስርዓት ለአፍሪካ በርካታ እድሎችን ይዞ መጥቷል ያሉት ምክትል ሊቀመንበሯ ይህን መልካም አጋጣሚ ለመጠቀም እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። አምባሳደር ማሊካ ዓለም አቀፍ አጋሮች አፍሪካ የዓለም የፋይናንስ ስርዓት እኩልነት የሰፈነበት እንዲሆን እና በተባበሩት መንግስታት የጸጥታ ምክር ቤት ውክልና እንድታገኝ እያነሳች ያለው ፍትሃዊ ጥያቄ እና እውነተኛ መሻት እንዲደግፍ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። አፍሪካ ከዓለም ጋር ያላት ትብብር በጋራ መከባበር እና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸው አፍሪካ ስታድግ የዓለም ብልጽግና እና መረጋጋት ይረጋገጣል ሲሉም ተናግረዋል።
ሐተታዎች
ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 306
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም። በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል። የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል። በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል። በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል። በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 511
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
"ያሆዴ"- ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት
Sep 28, 2025 603
(በማሙሽ ጋረደው - ከኢዜአ ሆሳዕና ቅርንጫፍ) የሀዲያ የአዲስ ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው። ለማህበራዊ የህይወት አመራር ጉልህ አስተዋጾም ስላለውም በሀዲያዎች ዘንድ በየዓመቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል፡፡ "ያሆዴ" ያለፈውን አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲስ ዘመን የሚቀበሉበት፤ የመጻኢ ተስፋ ብስራትና የልምላሜ ምልክትም ጭምር ተደርጎም ይቆጠራል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሲቀርብ የሀዲያ ተወላጆችና የበዓሉ ተሳታፊዎች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከያሉበት ወደአካባቢው በመምጣት ይሰባሰባሉ፡፡ በዘንድሮ የያሆዴ በዓልም የሀድያ ተወላጆች የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ በተዘጋጀ ስፍራ (ነፈራ) ተሰባስበው በዓሉን በድምቀት አክብረውታል፡፡ በበዓሉ አከባበር ያለፈው ዓመት ስኬትም ይገመገማል፤ በአዲሱ ዓመትም የተሻለ ተሰርቶ ስኬት እንዲመዘገብ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት ይካሄዳል። ሊተገበር የሚችል ዕቅድም ይታቀዳል፡፡ በግልና በቤተሰብ የመጡ ስኬቶች በጋራ በመሆን ይገመገማሉ። የበረቱና ውጤት ያስመዘገቡም እንዲበረታቱ ይደረጋል። ለዚህም ነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው የሚባለው። ሰዎች እንዲሰሩና ስኬት እንዲያስመዘግቡ የሚያበረታታ እሴት አለው። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፋን ቦጋለ እንደሚሉት የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል "ያሆዴ" ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት ነው፡፡ ከነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የበዓሉ መቃረብን የሚያበስሩት ታዳጊ ልጆች ናቸው። ልጆቹ የዋሽንት (ገምባቡያ) ድምጽ ማሰማት ከጀመሩ በጉጉት የሚጠበቀውን የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል መድረሱ ምልክት ነው። በዓሉ ሀድያዎች አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበት ወቅት ነው። በዓሉ የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት በመሆኑም የተለየ ትርጉምና ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች ተራርቀው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት ከያሉበት ይሰባሰባሉ። በዓሉ በአማረ መልኩ እንዲከበርም ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻቸውን ያከናውናሉ። አባውራዎች ለበዓሉ ሠንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በቱታ ወይም በቅርጫ ቡድናቸው አማካኝነት እየቆጠቡ ይቆያሉ። እንዲሁም ለእንስሳት የሚሆን የግጦሽ ሳር የሚያበቅል ቦታ ከልለው ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሚሆነበት ምክንያት ደግሞ በዓሉ በሚከበርበት ሰሞን የሰው ልጅ ይቅርና እንስሳትም መጥገብ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ እማውራዎች ከበዓሉ ሦስትና አራት ወራት አስቀድመው እንሰት በመፋቅ ቆጮና ቡላ ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም ከአካባቢው እናቶች በጋራ በመሆን (ዊጆ) የተሰኘ የቅቤ እቁብ በመግባት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ማጠራቀም ይጀምራሉ፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ ለአተካናና ለሥጋ መብያ ናቀሮ ወይም ዳጣን እንዲሁም የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት ድርሻ የእናቶች ነው፡፡ ለበዓሉ የቤት ውስጥና የውጭ ግርግዳን በቀለምና በተለያዩ ጌጣጌጦች የማስዋብ ሃላፊነት ደግሞ የልጃገረዶች ነው። ወጣት ወንዶች ከነሀሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚያሳዩዋቸውን ግንድ በመቁረጥ ለምግብ ማብስያ እንዲውል ፈልጠው ያዘጋጃሉ። በሀዲያዎች አጠራር ለችቦ የሚሆን እንጨት ወይም ጦምቦራ ከጫካ ለቅመው አስረው እንዲደርቅም ያስቀምጣሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት የሚያደርገው ጥረት በዓሉ በስኬትና በድምቀት እንዲከበር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በዚህም ያሆዴ ከተናጠል ይልቅ ትብብርን የሚያጠናክር ነው ማለት ይቻላል። እሴቱ በትብብር መድመቅ እንደሚቻልም የሚያሳይ ነው። ይህን ሀሳብ የሚጋሩት አቶ መስፍን የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል በምንም ሁኔታ መነጣጠል የማይቻል ትስስርን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ። ሀገራዊ አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር ዘመናትን የተሻገረና ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ባህላዊ እሴት ያለው መሆኑንም ይናገራሉ። በዓሉ ሊከበር ጥቂት ቀናት ሲቀረው አባውራዎች በቅርጫ ማህበራቸው አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ የእርድ በሬ ይገዛሉ። በዚህ ወቅት ገንዘብ ማዋጣት ያልቻሉ የቅርጫ አባላት እህል በሚደርስበት ወቅት ለመክፈል ተስማምተው በሬውን በዱቤ እንዲገዙ ይደረጋል፡፡ ይሄም የሚሆነው በያሆዴ በዓል አንዱ ሲበላ ሌላው ተመልካች መሆን ስለሌለበት ነው። እርስ በርስ መጨካከን እንዳይኖርና በዓሉን በአብሮነት ሁሉም ተደስቶ ማክበር እንዲችል ለማድረግ ነው። ከበዓሉ ዕለት በፊት ያለው የመጨረሻ ገበያም የእብድ ገበያ (መቻዕል ሜራ) የሚል ስያሜ አለው። ይሄ ሥያሜ ያገኘው በዓሉ ሲቃረብ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ውጥረት ታሳቢ በማድርግ ነው፡፡ በዚህ የእብድ ገበያ ህብረተሰቡ መገበያየት የሚጀምረው ጠዋት ማለዳ ጀምር ሲሆን የግብይት ሂደቱ የሚጠናቀቀው ደግሞ እኩለ ቀን ላይ ነው፡፡ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለመግዛትና የያሆዴ በዓል ከተከበረ በኋላ ለአንድ ወር ገበያ ስለማይቆም ይህን ታሳቢ ያደረገ ግብይት ለመፈጸም የግብይት ሂደቱ ጥድፊያ የበዛበት ሆኖ ይታያል። ያሆዴ በዓል መከበር የሚጀምረው በአተካን ሂሞ ወይም በአተካና ምሽት ሲሆን ይህም ከበዓሉ አንድ ቀን በፊት ያለው ምሽት ነው። ስያሜውን ያገኘው "አተካና" ከተሰኘና በያሆዴዎች ዘንድ ለክብር እንግዳ እና በዘመን መለወጫ ከሚዘጋጅ ምግብ ነው። አተካና ከወተት፣ ከአይብ፣ ከቡላ፣ ከቅቤና ከሌሎች የቅመማ ቅመም ውጤቶች የሚዘጋጅ ምግብ ሲሆን በጣም ጣፋጭና የምግበ ፍላጎትን የሚጨምር ምግብ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ይሄንን የተለየ ምግብ ተሰባስቦ በአብሮነት በመመገብ በደመቀ መልኩ በዓሉን ማክበር ይጀምራል፡፡ የአካባቢው አባቶች በወጣቶች የተዘጋጀ የማቀጣጠያ እንጨት (ሳቴ) ይዘው ትልቅ በሚባሉ አባውራ ቤት ደጃፍ ወደ ተዘጋጀው የችቦ ደመራ (ጦምቦራ) ቦታ ይመጣሉ:: የሀገር ሽማግሌች አዲሱ ዓመት የብርሃን ዓመት እንዲሆን፤ ለሀገርና ለህዝቦቿ ሰላም እንዲጸና፤ አብሮነት እንዲጠናከር፣ ሰላምና ፍቅር እንዲነግስ ፈጣሪያቸውን ከተማጸኑ በኋላ ችቦውን በእሳት ይለኩሳሉ፡፡ ችቦው ከተለኮሰ በኋላ የአካባቢው ወጣቶች ተሰባስበው ያሆዴ …ያሆዴ! …ያሆዴ! በማለት እየጨፈሩ ያነጋሉ ይጨፍራሉ:: በሀድያዎች ዘንድ "ያሆ" ማለት የአዲስ ዓመት መግባትን ተከትሎ ማብሰሪያ ጭፈራ ሲሆን "ኤዴ" ማለት ደግሞ አገናኝ ማለት ነው፡፡ በያሆዴ በዓል የእርድ ሥነ ስርዓት ለማከናወን ነዋሪዎች የሚሰበሰቡበት ስፍራ "ነፈራ" የሚል ስያሜ አለው። የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሰፋ ያለ ቦታ ሰሆን በተለያዩ የጥላ ዛፎች የተዋበና ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀም ነው። በእለቱ ለእርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኋላ የባህል ሽማግሌዎች የበሬውን ሻኛ በሰርዶ ሳር ለጋ ቅቤ ይቀባሉ፤ ወተትም ያፋሱበታል፡፡ ይህ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ጋቢማ የሚባል ሲሆን (የመልካም ምኞት) መግለጫ ስነ ስርዓትም ነው፡፡ ይህም ሥነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም "ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሀገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን " እያሉ በአባቶች ምርቃት ከተካሄደ በኋላ የእርድ ስነ ስርዓት ይከናወናል፡፡ የእርድ ሥነ ስርዓቱ የተከናወነበት ቤት እማወራ አስቀድመው ባደረጉት ዝግጅት መሰረት ቅቤ፤ (ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ) እንዲሁም ከታረደው የበሬ ሥጋ አርዚ ማራ (ቅምሻ) ይወሰድና ክትፎ ከተዘጋጀ በኋላ በጋራ እየበሉ እየተጫወቱ ይውላሉ፡፡ በዚህም በቅርጫ ሥጋው ላይ ከሚሳተፉት የቤተሰብ አባላት ውጪ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችም ጭምር አብረው በመብላት በመጠጣት በዓሉን በአንድነት ያሳልፋሉ፡፡ ቀሪውን የቅርጫ ሥጋም አባላቱ ተከፋፍለው ወደ እየቤታቸው ይወስዱታል፡፡ በዓሉ አብሮ የመብላት፣ የመጠጣት፣ የመጠያየቅ፣ ችግርንና ግጭትን በጋራ ተወያይቶ የመፍታት፣ መፈቃቀርና መተሳሰብን የሚፈጥር፣ አቅመ ደካሞችና የተቸገሩ የሚረዱበት የአብሮነት መገለጫ በመሆኑ በተለየ መልኩ ይከበራል፡ ከእርድ ሥርዓቱ በኋላ በማግስቱ ልጆች አደይ አበባ (ዘራሮ) ይዘው ወደ ወላጆቻቸው እየጨፈሩ ይመጣሉ። የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባላሉ። ከስጋውም፣ ከቦርዴውም፣ ከአተካናውም እንዲመገቡ ያደረጋል። ይህ ስነ ስርዓትም ሚክራ ይባላል። በያሆዴ የዘመን መለወጫ በዓል ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ሥጋና አደይ አበባ ጭምር ይዘው ይሄዳሉ። በዓሉ ያላገቡ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ለአዲስ ህይወት ጅማሬ የሚያበስሩበት በመሆኑን የተለየ ድባብ አለው፡፡ የያሆዴ በዓል ካሉት እሴቶች አንዱ የህብረተሰቡን የአካባቢ ልማት ተሳትፎ ማበረታታት ተጠቃሽ መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ዕሴቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናቅቀው ለማህበረሰብ ጥቅም እንዲውሉ ጭምር አቅም እየሆነ መምጣቱን ነው የሚናገሩት።ይህ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የማህበራዊ መስተጋብር መጋመጃ የሆነው በዓል እሴቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል መስራት ይገባል። እሳቸው እንዳሉት በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማስቻል እየተሰራ ነው፡፡ ለዚህም መምሪያው ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ዕሴቱን የመሰነድና ምርምሮች ማካሄድን ጨምሮ እያከናወናቸው ያሉ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።
80ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ እና የኢትዮጵያ ተሳትፎ
Sep 27, 2025 725
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ግዙፉና ጉምቱው የዓለም የብዝሃወገን ዲፕሎማሲ መድረክ ነው። 80ኛው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ከጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም አንስቶ “ደህናነት በአብሮነት፤ 80 ዓመታት እና ከዚያ በላይ ለሰላም፣ ለልማት እና ለሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። የጠቅላላ ጉባኤው አካል የሆነ ከፍተኛ የምክክር እና ክርክር መድረክ ከመስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተደረገ ነው። ከሰላም እስከ አየር ንብረት ለውጥ፣ ከዘላቂ ልማት እስከ ዲጂታል አካታችነት፣ ከሰብዓዊነት እስከ የዓለም የኢኮኖሚ አወቃቀር፣ በዓለም መድረክ ፍትሐዊ ውክልናን ከማግኘት እስከ ዓለም በቀጣይ ምን ትሆን? ድረስ በርካታ ጉዳዮች ተነስተው ውይይቶችና ክርክሮች በማድረግ ለወደፊቱ ይበጃሉ የተባሉ ሀሳቦች በመነሳት ላይ ይገኛሉ። በጉባኤው ይፋዊ መክፈቻ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ባደረጉት ንግግር ዓለም በተለያዩ ሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች፣ ድህነት፣ ረሃብ፣ ጦርነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣የኢኮኖሚ ቀውስ እየተፈተነች ባለበት ወቅት የሚከበረው የተመድ 80ኛ ዓመት አባል ሀገራት ከመቼውም ጊዜ በላይ አብሮነታቸውን በማጠናከር የተሻለች ዓለም ለመፍጠር በጋራ መሥራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል። የተመድ ሥርዓትንና መዋቅር 21ኛው ክፍለ ዘመን በሚመጥን ልክ መለወጥ እንደሚገባ አመልክተዋል። ዋና ፀሐፊው ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምርጫውን ሰላም፣ ፍትህ ዘላቂ ልማት እና ሰብአዊ ክብር ሊያደርግ እንደሚገባና ለተግባራዊነቱም ቁርጠኝነት እንዲያሳይ ጥሪ አቅርበዋል። በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በጠቅላላ ጉባዔው ላይ ተሳትፎ እያደረገ ነው። ልዑካን ቡድኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራን ጨምሮ ከፍተኛ ባለስልጣናትን አካቷል። ኢትዮጵያ በጉባዔው ላይ የራሷን ብሔራዊ ጥቅሞች እና የአፍሪካን ጥቅሞች በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ንቁና ጠንካራ ተሳትፎ እንደምታደርግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ከዋናው ጉባዔ ተሳትፎ በተጨማሪ በርካታ የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን የጎንዮሽ የውይይት መድረኮች ላይም ኢትዮጵያ የራሷን ብሄራዊ ጥቅሞች ቅድሚያ እየሰጠች እንደምትሳተፍም አመልክዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከጉባኤው ጎን ለጎን ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ጋር ተወያይተዋል። ዋና ፀሐፊው ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠናቃ በመመረቋ ፣ የአየር ንብረት ጉባዔ እና ሌሎች ፕሮጀክቶችን በማስተናገድ ላስመዘገበችው ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። ሁለቱ ወገኖች በቀጣናው እና በሌሎች ጉዳዮች ላይም ተወያይተዋል። በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ ከተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ፕሬዝዳንት አናሌና ባርቦክ ጋር ተወያይተዋል። ሁለቱ መሪዎች በወቅታዊ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች እና በባለብዙ ወገን ግንኙነት ላይ እያሳደረ ስለሚገኘው ተጽዕኖ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ የባለብዙ ወገን ግንኙነት እና የጋራ ደኀንነት መርሆዎችን ለማስጠበቅ የጋራ ጥረቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በቅርቡ የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የተመድ ዘላቂ ልማት ግቦችን ከማሳካት ረገድ በተለይም ግብ ሰባትን ለማሳካት ግድቡ ንጹሃ የኃይል አቅርቦት ከማሳደግ አኳያ ያለውን ፋይዳ ገልጸዋል። ፕሬዝዳንት አናሌና ባርቦክ በበኩላቸው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተር መርሆዎችን ማክበር እና መጠበቅ ለዓለም ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያ ልማት፣ ቀጣናዊ ሰላም እና ደኀንነትን ጨምሮ በተለያዩ ቀጣናዊ የትኩረት መስኮች ላይም መክረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ ከጉባኤው ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ጋር የሁለትዮሽ ውይይቶችን እያደረጉ ይገኛል። አምባሳደር ሃደራ ከደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መንደይ ሲማያ ኩምባ የኢትዮጵያ እና ሱዳን የሁለትዮሽ ኢኮኖሚያዊ ግፍንኙነት ማጠናከር እንዲሁም በቀጣናዊ እና በባለብዙ ወገን የትብብር መድረኮች የተባበረ አቋም እንዲኖራቸው ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መክረዋል። ከሞዛምቢክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሪያ ማኑኤላ ዶስ ሳንቶስ ሉቃስ ጋርም ተወያይተዋል። ሽብርተኝነትን መከላለከል፣ አቪዬሽን እና ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። አምባሳደሩ ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ ባለሥልጣን አምባሳደር ጆናታን ፕራት ጋር በሀገራቱ የጋራ ፍላጎቶች ላይ ተወያይተዋል። ሁለቱ ወገኖች በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የንግድ ግንኙነት ማሻሻል የሚያስችሉ ሥራዎችን ለማከናወን ተስማምተዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ከአውሮፓ ከአውሮፓ ሕብረት የውስጥ ጉዳይ እና የፍልሰት ኮሚሽነር ማግነስ ብሩነር ጋርም የተወያዩ ሲሆን ሁለቱ ወገኖች ዓለም አቀፍ ፈተና በሆኑ ከፍልሰት ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። አምባሳደሩ ከተባበሩት አረብ ኢምሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሼክ ሻክቦት ቢን ናህያን አል ናህያን ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የበለጠ በሚያጠናክሩ ዕድሎች እንዲሁም በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር የበለጠ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። አምባሳደር ሃደራ አበራ ከኩባ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሩኖ ሮድሪጌዝ ፓሪላ ጋር በሁለትዮሽ ትብብር ዙሪያ መክረዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ከአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጄሁን ቤራሞቭ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው አገራት መሆናቸውን በመጥቀስ ሁለቱ አገራት በተለይ በኢኮኖሚ ዘርፎች ይበልጥ ተቀናጅተው ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ገልፀዋል። ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው ሀገራቱ በንግድ፣ በኢንቬስትመንት፣ በቱሪዝም በግብርናና በትምህርት ዘርፎች እንዲሁም በባለብዙ ወገን መድረክ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል። ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ጉባኤው ጎን ለጎን ባሉ የጎንዮሽ ውይይቶች ላይ እየሳተፈች ይገኛል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተሳተፉበት መድረክ ኢትዮጵያ የአፍሪካን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ማስፋት አላማ ያደረገው “Mission 300” ኢኒሼቲቭ ተቀላቅላለች። በዓለም ባንክ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ የሚመራው ኢኒሼቲቭ እ.አ.አ በ2030 በአፍሪካ የሚገኙ 300 ሚሊዮን ዜጎችን በኤሌክትሪክ ኃይል የማስተሳሰር ውጥን ያለው ነው። ፕሮጀክቱ የአፍሪካ መንግስታት፣ የግሉ ዘርፍ እና የልማት አጋሮችን ያሳተፈ ሲሆን በአፍሪካ አስተማማኝነቱ የተረጋገጠ፣ አካታች እና ተመጣጣኝ የኢነርጂ አቅርቦትን ተደራሽ በማድረግ የኢኮኖሚ እድገት እና ቀጣናዊ ትስስርን የማጠናከር አላማንም አንግቧል። ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ያላትን እምቅ አቅም ለመጠቀም እና ቀጣናዊ የኃይል ትስስሯን ለማሳደግ ወሳኝ ሚና እንዳለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ የንጹህ ኢነርጂ ሽግግር ውስጥ ያላትን የመሪነት ሚና እንደሚያሳድግና አፍሪካ ከኢነርጂ ድህነት የማላቀቅ እና ዘላቂ ልማትን የማረጋገጥ ትልም ለማሳካት እንደሚያግዝም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በአፍሪካ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (ሲዲሲ አፍሪካ) ኮሚቴ አባል የመሪዎች ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል። ሚኒስትር ዴኤታው በስብሰባው ላይ ኢትዮጵያ የጤናን ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥ የሀብት ማሰባሰብ እና ፈጠራ የተሞላበት የፋይናንስ ግኝት እንደምትከተል አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በጠቅላላ ጉባኤው ብሔራዊ ጥቅሞች እና የአፍሪካን ጥቅሞች በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ንቁና ጠንካራ ተሳትፎ ማድረጓን እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ገልጸዋል። በጉባኤው ላይ የኢትዮጵያን ልዑክ የመሩት ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የጉባኤው አካል በሆነው ከፍተኛ የምክክር እና ክርክር መድረክ ላይ ንግግር አድርገዋል። ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው በመልክዓ ምድራዊ ሁኔታዎች ምክንያት የትኛውም ሀገር የእድገት፣ የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ዕድሎች ዝግ መሆን የለበትም ሲሉ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር በመሆን በቀይ ባሕር እና በሕንድ ውቅያኖስ አካባቢ የሚገኙ ሁሉም ሀገሮች እኩል ልማት እና ደኀንነትን ማረጋገጥ ወደሚያስችል ሁለንተናዊ አሠራር እንዲዘረጋ ትሠራለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ይህንን ሕጋዊ ፖሊሲዋን ለማሳካትም የዲፕሎማሲያዊ እና ሰላማዊ አማራጮችን እንደምትከተል አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ፕሬዝዳንቱ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤትን ለማሻሻል አስቸኳይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። በማሻሻያውም ለአፍሪካ ውክልና በምክር ቤቱ በሁለቱም በኩል ቅድሚያ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበው፤ ለአፍሪካ የረጅም ጊዜ የፍትሕ መሻት ጥያቄ አቋራጭ ወይም ግማሽ መፍትሔ እንደሌለ አስገንዝበዋል። ከታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘም፤ የናይል ወንዝ የትብብር ማዕቀፍ በፈረንጆቹ ጥቅምት 2024 ወደ ተግባር መግባቱን እና የናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን ወደ መቋቋም ደረጃ መቃረቡን አስረድተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ መመረቁ፤ በኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ላልሆኑ ኢትዮጵያውያን ንጹህ የኃይል ምንጭ እንዲያገኙ የሚያደርግ መሆኑን አስገንዝበዋል። ግድቡ በከባድ የውኃ እጥረት ውስጥ ለሚኖሩ ወገኖቻችን ንጹህ ውኃ ለማቅረብ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና አጠቃላይ ልማትን እውን ለማድረግ አቅማችንን ያሳድጋል ብለዋል ፕሬዚዳንቱ። ግድቡ ለሰፋፊ ክልላዊ ትስስር ተስፋን የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ 1945 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሲመሰረት መስራች አባል ከነበሩት ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ይህም ኢትዮጵያ የባለብዝሃ ወገን እና ዓለም አቀፍ ትብብር ያላትን የማይናወጥ አቋም እና የጸና ቁርጠኝነት በግልጽ የሚያሳይ ነው። ኢትዮጵያ በዘንድሮው ጉባኤ ሰላም፣ ደህንነት፣ ዘላቂ ልማት እና የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ በዓለም አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ያራሷ እና የአፍሪካን ድምጽ በማሰማት የነቃ ተሳትፎ እያደረገች ትገኛለች። 80ኛው የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም ይጠናቀቃል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 825
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1640
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2432
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2592
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 148
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 215
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6077
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4555
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ኢሬቻ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ማንሰራራት!
Oct 3, 2025 616
ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ሰዎች በክረምት ወቅት ከሚከሰት መለያየትና መራራቅ በኋላ ዳግም የሚገናኙበት፣ በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት ዕለት ነው። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። ኢሬቻ የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ጥብቅ ቁርኝት የሚገለጽበት የገዳ ስርዓት አንዱ አካል ነው፡፡ የኢሬቻ እሴቶች ጠንካራ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ያላት ሀገር ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው። አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ አብሮነት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ዕርቅ እና ሌሎችም ተጠቃሽ የመልካም እሴቶች መገለጫ ነው። በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አንዱ እሴት ኢሬቻ ሲሆን፤ ለሀገር ማንሠራራትና ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሠረት ይሆናል፡፡ ኢሬቻ አብሮነት የሚጸናበት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ይበልጥ የሚጎላበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጎለብትበት፣ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ማሰሪያ ከፍ ያለ በዓል ነው፡፡ ኢሬቻ በጋራ የሚያከብሩትና የዓለም ቱሪስቶች የሚታደሙበት ሲሆን፤ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል አከባበር ሀገራዊ ማንሰራራት በተግባር የተረጋገጠበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ዓለም የኢትዮጵያን መቻል በተግባር ባየበትና ሌሎች ለሀገር ማንሰራራት ዕውን መሆን መሠረት የሚጥሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኘሮጀክቶች ይፋ በተደረጉበት ማግስት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡ በዓሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመላው ኢትዮጵያዊያንን ሕብረት የሚንጸባረቅበት ሆኖ በተለያዩ አከባቢዎች በድምቀት እየተከበረም ይገኛል፡፡ በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Waaqa Uumaa, Waaqa Uumamaa ፍጥረትን የፈጠርክ ፈጣሪ Gurraacha garaa garbaa የእውነትና የሰላም አምላክ! Dogoggora nu oolchi ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! Dacheef nagaa kenni ለምድራችን ሰላም ስጥ! Laggeenif nagaa kenni ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! Olota keenyaaf nagaa kenni ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! . . . Loowan keenyaaf nagaa kenni " ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "አሜን! አሜን! አሜን!” ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 25 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ " ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት " በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" Irreecha Birraa (በውኃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን፤ በዓመቱ አጋማሽ ላይ "ኢሬቻ ቱሉ" Irreecha Arfaasaa ደግሞ በተራራማ ቦታ ይከበራል። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ነው። የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመምጣቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ይህ ከማህበራዊ መስተጋብር አኳያም ሰዎች የሚሰባሰቡበትና የሚገናኙበት ነው። ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ብርሃን (ብራ) ስለደረሰ ለዚያ ምልክት ይሆን ዘንድ የለመለመ እርጥብ ሣር ይዘው ወደ ወንዝ በመውረድ ንጹህ ውሃ ውስጥ እየነከሩና እየረጩ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ አብሮነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። ኢሬቻ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው "ዋቃ" "Waaqa" ምስጋናውን ለማድረስ የሚከበር ሲሆን፤ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲከበር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። ኢሬቻ የወንድማማችነትና የአንድነት አርማ ሲሆን፤ የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ፣ የህብረ ብሔራዊ አብሮነት ማስተሳሰሪያም ጭምር ነው፡፡ በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይበዛል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል፣ አንድነት ይጸናል። ኢሬቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ነው። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ስለሆነም ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር እንዲህ እያሉ ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። የበዓሉ ታዳሚዎች ከዋዜማው ጀምሮ በሆረ ፊንፊኔና በሆረ ሀርሰዲ በመሰባሰብ፤ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎችን በማዜምና ምስጋና በማቅረብ አድረው በነጋታው ዋናውን የምስጋና በዓልም ያከናውናሉ፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የደስታና የምስጋና ምልክት የሆነውን ባህላዊ ነጫጭ ልብስ ለብሰው፣ ባህልን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ሁነቶችን በመከወን ልዩ ልዩ ዜማዎችን በማዜም፣ ግጥሞችን በማቅረብ፣ ወደ ፈጣሪ በመጸለይ እና ምስጋና በማቅረብ ሥርዓቱን ያከናውናሉ፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ከማቀራረብና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጾኦ ያለው ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገር የመጡ ልዑካን በበዓሉ ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። የኢሬቻ በዓል ለቱሪዝም ፍሰት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ጉልህ ነው፤ በርካታ የባህር ማዶ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የሚታደሙበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ ሲሆን፤ ዘርፉን በማጠናከር እና ብሔራዊ ልማትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚናንም የሚጫወት ነው፡፡ ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!
በትግራይ ክልል የመስቀል በዓል አከባበር
Sep 27, 2025 702
የመስቀል በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በልዩ ድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ ነው። በዓሉ እንደየአካባቢው ባህላዊና ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል። በትግራይ ክልልም የመስቀል በዓል እንደሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሁሉ በናፍቆት ከሚጠበቁና በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት ተርታ ይመደባል። ለዚህም ሲባል የተለያዩ ዝግጅቶች ከበዓሉ ዋዜማ በፊት እንዲጠናቀቁ የሚደረግ ሲሆን፥ በተለይ በየዓመቱ መስከረም 16 እና 17 ዘመድ አዝማድ ተጠራርተው የሚገናኙበት የፍቅርና የአብሮነት በዓል ሆኖ ይከበራል። የክርስቶስ ግማደ መስቀል በንግስት ኢሌኒ አማካኝነት መገኘቱን በማሰብ በየዓመቱ መስከረም አጋማሽ ላይ የሚከበረው የመስቀል በዓል የመስቀል ኃያልነት፣ እውነት በተደበቀበት ለዘላለም እንደማይቀርና ፍቅርን አብዝቶ የሚሰበክበት ከዚህ ባለፈም እርቅ የሚወርድበትና ደስታ የሚገለጽበት አጋጣሚ መሆኑም ይገለጻል። በትግራይ የበዓሉን ታላቅነትና ክብር ለማድመቅ ምእመናን ጽዱ ልብስ ለብሰውና የተለያዩ ዝማሬዎችን በማሰማት ደመራ ወደሚደመርበት ሥፍራ ችቦ ይዘው በመሄድ ደምራውን በማቀጣጠል የሚያከበሩት ሲሆን፣ በእለቱ የቤት እንስሳት ጭምር ቀንዳቸውና ጀርባቸው ላይ ቅቤ ተቀብተው እንዲያርፉ ይደረጋል። ዘመድ አዝማድ፣ ጎረቤታሞች፣ አብሮ አደጎችና የበዓሉ ታዳሚ እንግዶችም ተሰባስበው ማለዳ ላይ ገንፎ በማዘጋጀት ይመገባሉ። የእንስሳት እርድ በማከናወን ባህላዊ መጠጦችን በማዘጋጀት በዓሉን የፍቅር፣ የመሰባሰብ፣ የአንድነትና ተካፍሎ የመብላት በዓል መሆኑን በተግባር የሚያሳይበት ክስተት ሆኖ ያልፋል። "ዓኾይ ዓኾኾይ" የጎመን ምንቸት ውጣ የገንፎ ምንቸት ግባ በማለትም ችቦ ተሎኮሶ በየቤቱ በመዞር የምረቃ እና ለሚቀጥለው ዓመትም በሰላምና ደስታ እንዲሁም እድሜና ጤናን በመመኘት ይከወናል። የአደባባይ በዓል የሆነው የመስቀል በዓል በዝማሬ፣ በሆታና እልልታ የሚገለጽ ሲሆን፤ ወርሃ መስከረም እሸት አሽቶ አበቦች አብበውና ምድር ልዩ ልምላሜን ተላብሶ የሚታይ በመሆኑ ልክ በታሪኩ እንደሰፈረው የሰላም፣ የእውነትና የአንድነት በዓል መሆኑን በተግባር የሚታይበት ነው።