ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጉብኝት ተመልሰው በቀጥታ ወደ አርባምንጭ አቀኑ
Mar 14, 2026 26
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጉብኝት ተመልሰው በቀጥታ ወደ አርባምንጭ ማቅናታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በአርባ ምንጭ ዙሪያ እና በመላው ጋሞ ዞን በደረሰው አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ሐዘናቸውን ለመግለጽ እና የሚከናወኑ የድጋፍ ስራዎችን እንደሚገመግሙም ገልጿል። ለቀናት የዘለቀው ከባድ ዝናብን ተከትሎ በአካባቢው የተከሰተው ጎርፍ፤ የመሬት መንሸራተት አደጋ የዜጎቻችንን ህይወት ቀጥፏል፣ በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል ነው ያለው ጽህፈት ቤቱ በመልዕክቱ። ከመጠን በላይ የሞላው የኩልፎ ወንዝም መንደሮችን፣ ቤቶችን፣ የእርሻ ስፍራዎችን፣ የአካባቢ መሠረተ ልማትን ማውደሙን አስታውቋል። ማኅበረሰቡ በከባድ ሀዘን በሚገኝበት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የነፍስ አድን ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል ከተጎጂ ቤተሰቦች ጎን መቆም ይገባናል ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
ተመራቂዎች በመልካም ስነምገባርና በሃላፊነት ስሜት ህዝባቸውን ማገለግል ይጠበቅባቸዋል - ዶክተር ደረጀ ዱጉማ
Mar 14, 2026 18
ነቀምቴ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ተመራቂዎች በላቀ ሥነ-ምግባርና በኃላፊነት ስሜት ሕዝባቸውን ሊያገለግሉ እንደሚገባ የጤና ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ገለጹ። ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 792 ተማሪዎችን ዛሬ በደመቀ ሁኔታ አስመርቋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በበየነ-መረብ መልእክታቸውን ያስተላለፉት የጤና ሚኒስትር ደኤታው ዶክተር ደረጄ፣ ተመራቂዎች የቀሰሙትን ዕውቀት ከዘመኑ ጋር በማዛመድ ለሀገሪቱ የእድገት ጉዞ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይ የጤና ዘርፍ ተመራቂዎች፤ ሙያው ከፍተኛ ሰብአዊነትን የሚጠይቅ መሆኑን ጠቅሰው፣ የእናቶችንና የሕጻናትን ሕይወት የመታደግ ከባድ አደራ በላቀ ሥነ-ምግባርና በኃላፊነት ስሜት እንዲወጡ አስገንዝበዋል። የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ተስፋዬ ለማ(ዶ/ር) እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው በነቀምቴ፣ በሻምቡ እና በጊምቢ ካምፓሶቹ ብቁና የተማረ የሰው ኃይል በማፍራት በኩል ያለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት እየተወጣ ነው። ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ባገኙት ትምህርትና ልምድ ሕብረተሰባቸውን ለማገልገል ቆርጠው መነሳት ይገባቸዋል ብለዋል። የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ መሰረት ኃይሉ በበኩላቸው፤ ውጤቱ የቤተሰብና የመላው ማኅበረሰብ ድካም መሆኑን ገልጸዋል። በዕለቱ በሕክምና ትምህርት ክፍል 3 ነጥብ 5 ውጤት ያስመዘገበችው ዶክተር ሎዛ መድኃኒቴ እንደተናገረችው፣ በዩኒቨርሲቲው በቀሰመችው እውቀት ሴቶችና ሕጻናትን በተሻለ ሁኔታ ለማገልገል ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች። ሌላው 3 ነጥብ 87 ውጤት በማምጣት የዋንጫና የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኖ የተመረቀው ተማሪ ሳሙኤል ኃይሌ፤ ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀሙ ለውጤት መብቃቱን በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ባገኘው ልምድና ትምህርት ማኅበረሰቡን በትጋት ለማገልገል መዘጋጀቱን ተናግሯል። ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ካስመረቃቸው መካከል በመጀመሪያ ዲግሪ 661፣ በሁለተኛ ዲግሪ 125 እና የዶክትሬት ዲግሪ PhD) 6 ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል።
ትግራይ ክልል ለልማትና ሰላም ግንባታ የተሰለፉ ወጣቶችን ትፈልጋለች - አብረሃም በላይ (ዶ/ር)
Mar 14, 2026 33
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ትግራይ ክልል ለልማትና ሰላም ግንባታ የተሰለፉ ወጣቶችን ትፈልጋለች ሲሉ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) ገለጹ። በአዋሽ አርባ ጊዜያዊ የዲሞቢላይዜሽን ማዕከል፤ በሱዳን የቆዩ እና የሰላም አማራጭን ተቀብለው ወደ አገራቸው የተመለሱ፣ ከቀድሞ ህወሃት ጎን የነበሩና በተለምዶ አርሚ 70 እየተባሉ የሚጠሩ አባላት የተሃድሶ ሥልጠና ማጠቃለያ መርኃ ግብር ተካሂዷል። በመድረኩ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) እና የብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዲየር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ ተገኝተዋል። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) የሰላም አማራጭን በመከተል ወደ ሀገራቸው በመመለስ የተሀድሶ ስልጠና በመከታተላቸው አድንቀዋል። የፌዴራል መንግስት በትግራይ ሰላምን ለማፅናት እና ልማትን ለማረጋገጥ ያልሞከረው ሙከራ እንደሌለ ጠቁመው፤ ቆሞ ቀሩ የቀድሞ ህወሓት ቡድን ከህዝብ በላይ ነኝ በሚል እሳቤ አሁንም እንቅፋት እየሆነ መምጣቱን አብራርተዋል። ቡድኑ በሚያሰራጨው የሃሰት ወሬ ህዝቡ ሊደናገር አይገባም ያሉት ዶክተር አብርሃም፤ ከመንግስት ጎን ሆኖ ልማቱን እንዲያፋጥን ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ቆሞ ቀር ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየበት ወቅት ሀገር ከማልማት ይልቅ የግል ጥቅምን ያስቀደመ እንደነበር አስታውሰዋል። የፌዴራል መንግስት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት የሚጠበቅበትን ተግባራት ሁሉ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ወጣቱ ከግጭት አውድማ ወጥቶ ሰላምን መምረጡ ለራሱም፣ ለክልሉም ሆነ ለሀገሩ ትልቅ ስኬት መሆኑ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት ትግራይ ክልል የሚያስፈልጋት ለልማትና ለሰላም ግንባታ የተሰለፈ ወጣት እንጂ ለግጭት የሚማገድ እንዳልሆነም አስገንዝበዋል። በሀገሪቷ በማንኛውም አካባቢ የመስራትና የመንቀሳቀስ መብቱ የተጠበቀ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀድሞ የህወሓት ቡድን የሚነዙ የተሳሳቱ አሉባልታዎችን ውድቅ አድርገዋል። ትግራይን ወደ ፊት ማራመድ የሚቻለው በግጭት ሳይሆን ሰላምን መሠረት ባደረገ ኃይል ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል። የብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዲየር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ በበኩላቸው፤ እነዚህ ወገኖች ቀደም ሲል በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ያገለገሉ፣ በዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች የተሳተፉና በሱዳን ድንበር አካባቢ የነበሩ ናቸው ብለዋል። የሰላምን አማራጭ በመቀበል ወደ ማዕከሉ የመጡትን ዜጎች የመለየት፣ የማረጋገጥና የመመዝገብ ሥራ በጥንቃቄ ተከናውኖ ወደ ተሃድሶ ሥልጠና እንዲገቡ መደረጉን ነው ያስረዱት። የተሃድሶ ሥልጠና ዓላማ ከግጭት አስተሳሰብ ተላቅቀው የሰላምና የልማት ኃይል እንዲሆኑ ማድረግ አንዱ መሆኑን አመልክተው፤ እንዲሁም በማህበረሰቡ ውስጥ ሲቀላቀሉ ሰላምን የሚያፀኑ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው ብለዋል። በቀጣይም ሰፋፊና ጥልቀት ያላቸው የተሃድሶ ሥልጠናዎች እንደሚሰጡ ጠቁመዋል። የሰላም አምባሳደር በመሆን የሀገርን አንድነትና ልማት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስኬት በምሳሌነት የሚወሰድ ነው
Mar 14, 2026 26
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስኬት በምሳሌነት የሚወሰድ የልማት አጀንዳ መሆኑን በኢትዮጵያ የሕንድ አምባሳደር አኒል ኩመር ራይ ገለጹ። አምባሳደር አኒል ኩመር ራይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በርካታ ችግኞችን በመትከል የካርቦን ልቀትን መቀነስ የሚያስችል ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል። ከብክለት ነፃ የሆኑ የትራንስፖርት አማራጮችን በማስፋት በኩልም ለአየር ንብረት ተፅዕኖ የማይበገር አረንጓዴ የኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ወሳኝ እርምጃ እየወሰደች እንደምተገኝም አንስተዋል። የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስኬት በምሳሌነት የሚወሰድ የልማት አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የኢኮኖሚ ሥርዓት ግንባታም ለሌሎች የአፍሪካ እና የዓለም ሀገራት ተሞክሮ የሚወሰድበት መሆኑን ገልጸዋል። ሕንድም ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት በምታደርገው ጥረት ትብብሯን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። በቅርቡ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ የፕላስቲክ መያዣዎች ላይ የእግድ ውሳኔ መተላለፉ ለአካባቢ ደኅንነትና ሥነ-ምኅዳር ጥበቃ ጉልህ ፋይዳ ያለው ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም ሕንድ በአካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ሥርዓት ያላትን ልምድና ተሞክሮ በማጋራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ2 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ
Mar 14, 2026 31
አርባ ምንጭ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ2 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሃዲ፤ በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች የማገዝና የመደገፍ ስራ የሁሉም ሃላፊነት መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የ2 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታውቀዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ(ዶ/ር)፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል። ለወገን ደራሽ ወገን በመሆኑ ከህዝቡ ጎን በመሆን ድጋፍ እያደረጉ ላሉ ተቋማትና ግለሰቦች የላቀ ምስጋና አለን ብለዋል።
ፖለቲካ
ትግራይ ክልል ለልማትና ሰላም ግንባታ የተሰለፉ ወጣቶችን ትፈልጋለች - አብረሃም በላይ (ዶ/ር)
Mar 14, 2026 33
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ትግራይ ክልል ለልማትና ሰላም ግንባታ የተሰለፉ ወጣቶችን ትፈልጋለች ሲሉ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) ገለጹ። በአዋሽ አርባ ጊዜያዊ የዲሞቢላይዜሽን ማዕከል፤ በሱዳን የቆዩ እና የሰላም አማራጭን ተቀብለው ወደ አገራቸው የተመለሱ፣ ከቀድሞ ህወሃት ጎን የነበሩና በተለምዶ አርሚ 70 እየተባሉ የሚጠሩ አባላት የተሃድሶ ሥልጠና ማጠቃለያ መርኃ ግብር ተካሂዷል። በመድረኩ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) እና የብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዲየር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ ተገኝተዋል። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) የሰላም አማራጭን በመከተል ወደ ሀገራቸው በመመለስ የተሀድሶ ስልጠና በመከታተላቸው አድንቀዋል። የፌዴራል መንግስት በትግራይ ሰላምን ለማፅናት እና ልማትን ለማረጋገጥ ያልሞከረው ሙከራ እንደሌለ ጠቁመው፤ ቆሞ ቀሩ የቀድሞ ህወሓት ቡድን ከህዝብ በላይ ነኝ በሚል እሳቤ አሁንም እንቅፋት እየሆነ መምጣቱን አብራርተዋል። ቡድኑ በሚያሰራጨው የሃሰት ወሬ ህዝቡ ሊደናገር አይገባም ያሉት ዶክተር አብርሃም፤ ከመንግስት ጎን ሆኖ ልማቱን እንዲያፋጥን ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ቆሞ ቀር ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየበት ወቅት ሀገር ከማልማት ይልቅ የግል ጥቅምን ያስቀደመ እንደነበር አስታውሰዋል። የፌዴራል መንግስት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት የሚጠበቅበትን ተግባራት ሁሉ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ወጣቱ ከግጭት አውድማ ወጥቶ ሰላምን መምረጡ ለራሱም፣ ለክልሉም ሆነ ለሀገሩ ትልቅ ስኬት መሆኑ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት ትግራይ ክልል የሚያስፈልጋት ለልማትና ለሰላም ግንባታ የተሰለፈ ወጣት እንጂ ለግጭት የሚማገድ እንዳልሆነም አስገንዝበዋል። በሀገሪቷ በማንኛውም አካባቢ የመስራትና የመንቀሳቀስ መብቱ የተጠበቀ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀድሞ የህወሓት ቡድን የሚነዙ የተሳሳቱ አሉባልታዎችን ውድቅ አድርገዋል። ትግራይን ወደ ፊት ማራመድ የሚቻለው በግጭት ሳይሆን ሰላምን መሠረት ባደረገ ኃይል ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል። የብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዲየር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ በበኩላቸው፤ እነዚህ ወገኖች ቀደም ሲል በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ያገለገሉ፣ በዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች የተሳተፉና በሱዳን ድንበር አካባቢ የነበሩ ናቸው ብለዋል። የሰላምን አማራጭ በመቀበል ወደ ማዕከሉ የመጡትን ዜጎች የመለየት፣ የማረጋገጥና የመመዝገብ ሥራ በጥንቃቄ ተከናውኖ ወደ ተሃድሶ ሥልጠና እንዲገቡ መደረጉን ነው ያስረዱት። የተሃድሶ ሥልጠና ዓላማ ከግጭት አስተሳሰብ ተላቅቀው የሰላምና የልማት ኃይል እንዲሆኑ ማድረግ አንዱ መሆኑን አመልክተው፤ እንዲሁም በማህበረሰቡ ውስጥ ሲቀላቀሉ ሰላምን የሚያፀኑ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው ብለዋል። በቀጣይም ሰፋፊና ጥልቀት ያላቸው የተሃድሶ ሥልጠናዎች እንደሚሰጡ ጠቁመዋል። የሰላም አምባሳደር በመሆን የሀገርን አንድነትና ልማት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዱባይ ገዢ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ግርማዊ ሼኽ ሞሃሙድ ቢን ራሺድ አል መክቱም ጋር ተወያዩ
Mar 14, 2026 129
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዱባይ ገዢ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ግርማዊ ሼኽ ሞሃሙድ ቢን ራሺድ አል መክቱም ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳስታወቁት የዱባይ ገዢ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ግርማዊ ሼኽ ሞሃሙድ ቢን ራሺድ አል መክቱምን አግኝቼ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮቻችን እና ሕዝቦቻችን መካከል ስላለው ጠንካራ የቢዝነስ፣ ትምህርት እና ባህል ትስስር ተነጋግረናል ሲሉም ገልጸዋል። ከዚህች ጠንካራ፣ ውብ እና ጽኑ ከተማ ጋር ያለን ትስስር በቀጣይ ጉብኝቶችም ይጠናከራል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
ምርጫው የሀገርና የህዝብን ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ በስኬት እንዲጠናቀቅ በትብብር እየሰራን ነው − የፖለቲካ ፓርቲዎች
Mar 14, 2026 141
ዲላ፤ መጋቢት 5/2018 (ኢዜአ)፡-7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገርና የህዝብን ጥቅም ባስቀደመ መልኩ በስኬት እንዲጠናቀቅ በትብብር እየሰሩ መሆናቸውን በጌዴኦ ዞን የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መርሀግብር መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎቹ እጩዎቻቸውን ከማስመዝገብ ባለፈ የምርጫ ፕሮግራምና ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የጌዴኦ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ዋና ጸሐፊ ግርማ ሐጌ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በምርጫው በነጻነት ለመወዳደር የሚያስችል ሰፊ ምህዳርና ፉክክር ለማድረግ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። በተለይ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከጥሎ ማለፍ የፖለቲካ ፉክክር በመውጣት ሀገርን ለሚያሻግር ሀሳብና አተያይ ይበልጥ ትኩረት መደረጉን ጠቅሰው ይህም ኢትዮጵያን ለማጽናት ትልቅ እገዛ ይኖረዋል ብለዋል። ፓርቲው በምርጫው ተወዳድሮ አሸናፊ ለመሆን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለእዚህም የፓርቲውን የልማትና የመልካም አስተዳደር አማራጭ ሀሳቦች ለህዝብ በማቅረብ በሃሳብ የበላይነት ብቻ ለማሸነፍ በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ብለዋል። በእስካሁኑ የምርጫ ሂደት እጩዎቻቸውን ከማቅረብ ባለፈ የሀሳብ የበላይነት ለመያዝ የሚያስችል ጠንካራ ፉክክር እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። ምርጫው ተአማኒ፣ ነጻና በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ከማድረግ ባለፈ ዴሚክራሲያዊ ሥርአትን በሚያጎለብት መልኩ እንዲካሄድ ፓርቲው የበኩሉን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የሀገርና የህዝብን ክብር ባስቀደመ መልኩ እንዲጠናቀቅ በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆኑ ያነሱት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊና የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ የዞኑ ሰብሳቢ አቶ ተፈራ ጎበና ናቸው። ሰባተኛው ምርጫ የህዝብ ድምጽ የሚከበርበትና የሃሳብ የበላይነት ብቻ አሸንፎ ተቀባይነትን የሚያገኝበት ሆኖ እንዲጠናቀቅ በጋራ ምክር ቤቱ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በምርጫው አሸናፊ ለመሆን ጠንካራ ፉክክር ማድረግ እንደሚገባ ገልጸው፣ ምርጫው ሀገርን ያስቀደመና የህዝብን ድምጽ ያከበረ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጋራ ምክር ቤቱ የበኩሉን እንደሚወጣ አረጋግጥዋል። በብልጽግና ፓርቲ የጌዴኦ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ አቶ አዲሱ አየለ በበኩላቸው እንዳሉት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራዊያዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሰራ ነው። ምርጫው የተለያዩ ፓርቲዎች አማራጭ ሀሳብ በስፋት የሚንሸራሸርበት፣ የሀሳብ የበላይነት የሰፈነበትና ሀገር የምታሸንፍበት እንዲሆን ከፓርቲዎች ጋር በትብብር እየሰራን ነው ብለዋል። በተለይ የምርጫ ህጉን አክብሮ ከመንቀሳቀስ ባለፈ ህዝቡ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ መሰረት የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ቅስቀሳ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር )ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ፕሬዚዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተወያዩ
Mar 13, 2026 645
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ፕሬዚዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተወያይተዋል፡፡ የጸና ወዳጅነት፣ በመተማመን ላይ የተመሠረተ ትብብር! ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት፡፡ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በነበረኝ የስራ ጉብኝት ከፕሬዝዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተገናኝቼ ተወያይተናልም ብለዋል። ውይይታችን በኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ለረጅም ዘመናት የቆየውን ወዳጅነት በማጎልበት፤ ትብብር እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር ሲሉም ተናግረዋል። ለተደረገልኝ አቀባበል እና በሀገሮቻችን መካከል የፀና ወዳጅነታችንን የበለጠ ለማጠናከር ለተጋራነው የፀና አቋም ምስጋናዬ የላቀ ነውም ብለዋል።
እስካሁን ከ9 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል
Mar 13, 2026 317
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ከ9 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበው የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ የመራጮች ምዝገባን በተመለከተና በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ የካቲት 28 መጀመሩን አስታውሰዋል። በዚህም የመራጮች ምዝገባ በዲጂታል እና በማኑዋል እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል። ከምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት ጋር በተያያዘ ወደ ተቋቋሙ የምርጫ ጣቢያዎች መሰራጨቱን ገልጸው፤ እስካሁን ከ9 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበው የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል።
የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታውን ለማቀላጠፍ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች በንቃት ሊሳተፉ ይገባል
Mar 13, 2026 267
ሰመራ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታውን ለማቀላጠፍ በዘንድሮው ምርጫ ሴቶች በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ የአፋር ክልል ሴት አመራሮች ተናገሩ። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ካርዳችንን በመጠቀም የተሻለ ሃሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - ነዋሪዎች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በምርጫ ጣቢያዎችና በበይነ መረብ የመራጮች ምዝገባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአፋር ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኀላፊ ነስሮ ኡዳ እንዳሉት፤ የክልሉ ሴቶች በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ሊሳተፉ ይገባል። በተለይም የዴሞክራሲ ሰርዓት ግንባታውን ለማቀላጠፍና ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን በተሟላ ሁኔታ መለማመድ የሚቻለው ሴቶች በምርጫ ሂደት ላይ የሚያደርጉት ተሳትፎ ሲያሳድጉ መሆኑን ተናግረዋል። በምርጫው ለመሳተፍ ከወዲሁ ካርድ ሊወስዱ እንደሚገባ አሳስበዋል። የአፋር ክልል ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ፋጡማ ሃንፈሬ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ በዘንድሮው ምርጫ ሴቶች ተጠቃሚነታቸውንና ተሳታፊነታቸውን ያሳድጋል ብለው ያመኑትን ፓርቲ በንቃት መምረጥ ይጠበቅባቸዋል። ለዚህም የመራጮች ካርድን በጊዜ በእጃቸው መያዝ እንደሚገባቸው ተናግረዋል።
ተመዝግበን ካርድ የወሰድነው ለልማት ቅድሚያ የሚሰጥ ፓርቲን ለመምረጥ ነው
Mar 13, 2026 174
ወልቂጤ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተመዝግበው ካርድ የወሰዱት ለልማትና ሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መሆኑን የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ለኢትዮጵያ ሰላም፣ ልማትና እድገት ይበጃል ለምንለው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠት የምርጫ ካርድ እየወሰድን ነው -ወጣቶች በወልቂጤ ከተማ ምርጫ ክልል በሚገኙ 138 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል። ኢዜአ በወልቂጤ ከተማ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች፤ ተመዝግበን ካርድ የወሰድነው ለሀገሪቱ ልማትና ሰላም ቅድሚያ የሚሰጥ የፖለቲካ ፓርቲን ወደ ስልጣን ለማምጣት ነው ብለዋል ። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ አብድልማሊክ ሹሌ ፤ በምርጫው ለመሳተፍና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ይናገራሉ ። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገለጫ በመሆኑም በድምጻቸው ለሀገር ሰላምና እድገት ይበጃል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጅት ማድረጋቸውን ነው የተናገሩት። የከተማው ነዋሪ ወጣት በለጠ ሀብቱ፤ በጠቅላላ ምርጫው ሀገርን ያሳድጋል ብዬ ያመንኩበትን ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስጃለሁ ነው ያለው። በተለይ የወጣቶች ስብእና ግንባታ ላይ ትኩረት የሚሰጥ፣ የስራ አጥነት ችግርን የሚፈታና አማራጭ የልማት ፖሊሲን ይዞ የሚቀርብ የፖለቲካ ፖርቲን ለመምረጥ መዘጋጀቱን አመላክቷል። ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በሀገራዊ ምርጫው ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን የገለፁት ደግሞ የከተማው ነዋሪ ወይዘሮ አሰለፈች ይርጉ ናቸው። የመምረጥና መመረጥ መብት በሕገ-መንግስቱ ለዜጎች የተሰጠ ዴሞክራሲያዊ መብት ነው ያሉት ወይዘሮ አሰለፈች ሀገርን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ያሻግራል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወልቂጤ ምርጫ ክልል ስራ አስፈፃሚ አቶ ተገኑ ደመቀ፤ በምርጫ ክልሉ በሚገኙ 138 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። በሁሉም ጣቢያዎች መራጮች ካርድ የሚወስዱት በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዳስታወቀው የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም የሚካሄድ ሲሆን ለዚሁ የሚሆኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።
ፖለቲካ
ትግራይ ክልል ለልማትና ሰላም ግንባታ የተሰለፉ ወጣቶችን ትፈልጋለች - አብረሃም በላይ (ዶ/ር)
Mar 14, 2026 33
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ትግራይ ክልል ለልማትና ሰላም ግንባታ የተሰለፉ ወጣቶችን ትፈልጋለች ሲሉ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) ገለጹ። በአዋሽ አርባ ጊዜያዊ የዲሞቢላይዜሽን ማዕከል፤ በሱዳን የቆዩ እና የሰላም አማራጭን ተቀብለው ወደ አገራቸው የተመለሱ፣ ከቀድሞ ህወሃት ጎን የነበሩና በተለምዶ አርሚ 70 እየተባሉ የሚጠሩ አባላት የተሃድሶ ሥልጠና ማጠቃለያ መርኃ ግብር ተካሂዷል። በመድረኩ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) እና የብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዲየር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ ተገኝተዋል። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) የሰላም አማራጭን በመከተል ወደ ሀገራቸው በመመለስ የተሀድሶ ስልጠና በመከታተላቸው አድንቀዋል። የፌዴራል መንግስት በትግራይ ሰላምን ለማፅናት እና ልማትን ለማረጋገጥ ያልሞከረው ሙከራ እንደሌለ ጠቁመው፤ ቆሞ ቀሩ የቀድሞ ህወሓት ቡድን ከህዝብ በላይ ነኝ በሚል እሳቤ አሁንም እንቅፋት እየሆነ መምጣቱን አብራርተዋል። ቡድኑ በሚያሰራጨው የሃሰት ወሬ ህዝቡ ሊደናገር አይገባም ያሉት ዶክተር አብርሃም፤ ከመንግስት ጎን ሆኖ ልማቱን እንዲያፋጥን ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ቆሞ ቀር ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየበት ወቅት ሀገር ከማልማት ይልቅ የግል ጥቅምን ያስቀደመ እንደነበር አስታውሰዋል። የፌዴራል መንግስት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት የሚጠበቅበትን ተግባራት ሁሉ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ወጣቱ ከግጭት አውድማ ወጥቶ ሰላምን መምረጡ ለራሱም፣ ለክልሉም ሆነ ለሀገሩ ትልቅ ስኬት መሆኑ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት ትግራይ ክልል የሚያስፈልጋት ለልማትና ለሰላም ግንባታ የተሰለፈ ወጣት እንጂ ለግጭት የሚማገድ እንዳልሆነም አስገንዝበዋል። በሀገሪቷ በማንኛውም አካባቢ የመስራትና የመንቀሳቀስ መብቱ የተጠበቀ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀድሞ የህወሓት ቡድን የሚነዙ የተሳሳቱ አሉባልታዎችን ውድቅ አድርገዋል። ትግራይን ወደ ፊት ማራመድ የሚቻለው በግጭት ሳይሆን ሰላምን መሠረት ባደረገ ኃይል ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል። የብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዲየር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ በበኩላቸው፤ እነዚህ ወገኖች ቀደም ሲል በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ያገለገሉ፣ በዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች የተሳተፉና በሱዳን ድንበር አካባቢ የነበሩ ናቸው ብለዋል። የሰላምን አማራጭ በመቀበል ወደ ማዕከሉ የመጡትን ዜጎች የመለየት፣ የማረጋገጥና የመመዝገብ ሥራ በጥንቃቄ ተከናውኖ ወደ ተሃድሶ ሥልጠና እንዲገቡ መደረጉን ነው ያስረዱት። የተሃድሶ ሥልጠና ዓላማ ከግጭት አስተሳሰብ ተላቅቀው የሰላምና የልማት ኃይል እንዲሆኑ ማድረግ አንዱ መሆኑን አመልክተው፤ እንዲሁም በማህበረሰቡ ውስጥ ሲቀላቀሉ ሰላምን የሚያፀኑ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው ብለዋል። በቀጣይም ሰፋፊና ጥልቀት ያላቸው የተሃድሶ ሥልጠናዎች እንደሚሰጡ ጠቁመዋል። የሰላም አምባሳደር በመሆን የሀገርን አንድነትና ልማት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዱባይ ገዢ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ግርማዊ ሼኽ ሞሃሙድ ቢን ራሺድ አል መክቱም ጋር ተወያዩ
Mar 14, 2026 129
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዱባይ ገዢ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ግርማዊ ሼኽ ሞሃሙድ ቢን ራሺድ አል መክቱም ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳስታወቁት የዱባይ ገዢ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ግርማዊ ሼኽ ሞሃሙድ ቢን ራሺድ አል መክቱምን አግኝቼ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮቻችን እና ሕዝቦቻችን መካከል ስላለው ጠንካራ የቢዝነስ፣ ትምህርት እና ባህል ትስስር ተነጋግረናል ሲሉም ገልጸዋል። ከዚህች ጠንካራ፣ ውብ እና ጽኑ ከተማ ጋር ያለን ትስስር በቀጣይ ጉብኝቶችም ይጠናከራል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
ምርጫው የሀገርና የህዝብን ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ በስኬት እንዲጠናቀቅ በትብብር እየሰራን ነው − የፖለቲካ ፓርቲዎች
Mar 14, 2026 141
ዲላ፤ መጋቢት 5/2018 (ኢዜአ)፡-7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገርና የህዝብን ጥቅም ባስቀደመ መልኩ በስኬት እንዲጠናቀቅ በትብብር እየሰሩ መሆናቸውን በጌዴኦ ዞን የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መርሀግብር መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎቹ እጩዎቻቸውን ከማስመዝገብ ባለፈ የምርጫ ፕሮግራምና ማኒፌስቷቸውን ለህዝብ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የጌዴኦ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ዋና ጸሐፊ ግርማ ሐጌ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በምርጫው በነጻነት ለመወዳደር የሚያስችል ሰፊ ምህዳርና ፉክክር ለማድረግ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። በተለይ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከጥሎ ማለፍ የፖለቲካ ፉክክር በመውጣት ሀገርን ለሚያሻግር ሀሳብና አተያይ ይበልጥ ትኩረት መደረጉን ጠቅሰው ይህም ኢትዮጵያን ለማጽናት ትልቅ እገዛ ይኖረዋል ብለዋል። ፓርቲው በምርጫው ተወዳድሮ አሸናፊ ለመሆን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለእዚህም የፓርቲውን የልማትና የመልካም አስተዳደር አማራጭ ሀሳቦች ለህዝብ በማቅረብ በሃሳብ የበላይነት ብቻ ለማሸነፍ በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ብለዋል። በእስካሁኑ የምርጫ ሂደት እጩዎቻቸውን ከማቅረብ ባለፈ የሀሳብ የበላይነት ለመያዝ የሚያስችል ጠንካራ ፉክክር እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። ምርጫው ተአማኒ፣ ነጻና በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ከማድረግ ባለፈ ዴሚክራሲያዊ ሥርአትን በሚያጎለብት መልኩ እንዲካሄድ ፓርቲው የበኩሉን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል። 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የሀገርና የህዝብን ክብር ባስቀደመ መልኩ እንዲጠናቀቅ በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆኑ ያነሱት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊና የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ የዞኑ ሰብሳቢ አቶ ተፈራ ጎበና ናቸው። ሰባተኛው ምርጫ የህዝብ ድምጽ የሚከበርበትና የሃሳብ የበላይነት ብቻ አሸንፎ ተቀባይነትን የሚያገኝበት ሆኖ እንዲጠናቀቅ በጋራ ምክር ቤቱ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በምርጫው አሸናፊ ለመሆን ጠንካራ ፉክክር ማድረግ እንደሚገባ ገልጸው፣ ምርጫው ሀገርን ያስቀደመና የህዝብን ድምጽ ያከበረ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጋራ ምክር ቤቱ የበኩሉን እንደሚወጣ አረጋግጥዋል። በብልጽግና ፓርቲ የጌዴኦ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ አቶ አዲሱ አየለ በበኩላቸው እንዳሉት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራዊያዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሰራ ነው። ምርጫው የተለያዩ ፓርቲዎች አማራጭ ሀሳብ በስፋት የሚንሸራሸርበት፣ የሀሳብ የበላይነት የሰፈነበትና ሀገር የምታሸንፍበት እንዲሆን ከፓርቲዎች ጋር በትብብር እየሰራን ነው ብለዋል። በተለይ የምርጫ ህጉን አክብሮ ከመንቀሳቀስ ባለፈ ህዝቡ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ መሰረት የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ቅስቀሳ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር )ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ፕሬዚዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተወያዩ
Mar 13, 2026 645
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ፕሬዚዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተወያይተዋል፡፡ የጸና ወዳጅነት፣ በመተማመን ላይ የተመሠረተ ትብብር! ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት፡፡ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በነበረኝ የስራ ጉብኝት ከፕሬዝዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተገናኝቼ ተወያይተናልም ብለዋል። ውይይታችን በኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ለረጅም ዘመናት የቆየውን ወዳጅነት በማጎልበት፤ ትብብር እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር ሲሉም ተናግረዋል። ለተደረገልኝ አቀባበል እና በሀገሮቻችን መካከል የፀና ወዳጅነታችንን የበለጠ ለማጠናከር ለተጋራነው የፀና አቋም ምስጋናዬ የላቀ ነውም ብለዋል።
እስካሁን ከ9 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል
Mar 13, 2026 317
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ከ9 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበው የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ የመራጮች ምዝገባን በተመለከተና በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ የካቲት 28 መጀመሩን አስታውሰዋል። በዚህም የመራጮች ምዝገባ በዲጂታል እና በማኑዋል እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል። ከምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት ጋር በተያያዘ ወደ ተቋቋሙ የምርጫ ጣቢያዎች መሰራጨቱን ገልጸው፤ እስካሁን ከ9 ሚሊየን በላይ መራጮች ተመዝግበው የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል።
የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታውን ለማቀላጠፍ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች በንቃት ሊሳተፉ ይገባል
Mar 13, 2026 267
ሰመራ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታውን ለማቀላጠፍ በዘንድሮው ምርጫ ሴቶች በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ የአፋር ክልል ሴት አመራሮች ተናገሩ። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ካርዳችንን በመጠቀም የተሻለ ሃሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል - ነዋሪዎች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በምርጫ ጣቢያዎችና በበይነ መረብ የመራጮች ምዝገባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአፋር ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኀላፊ ነስሮ ኡዳ እንዳሉት፤ የክልሉ ሴቶች በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት ሊሳተፉ ይገባል። በተለይም የዴሞክራሲ ሰርዓት ግንባታውን ለማቀላጠፍና ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን በተሟላ ሁኔታ መለማመድ የሚቻለው ሴቶች በምርጫ ሂደት ላይ የሚያደርጉት ተሳትፎ ሲያሳድጉ መሆኑን ተናግረዋል። በምርጫው ለመሳተፍ ከወዲሁ ካርድ ሊወስዱ እንደሚገባ አሳስበዋል። የአፋር ክልል ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ፋጡማ ሃንፈሬ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ በዘንድሮው ምርጫ ሴቶች ተጠቃሚነታቸውንና ተሳታፊነታቸውን ያሳድጋል ብለው ያመኑትን ፓርቲ በንቃት መምረጥ ይጠበቅባቸዋል። ለዚህም የመራጮች ካርድን በጊዜ በእጃቸው መያዝ እንደሚገባቸው ተናግረዋል።
ተመዝግበን ካርድ የወሰድነው ለልማት ቅድሚያ የሚሰጥ ፓርቲን ለመምረጥ ነው
Mar 13, 2026 174
ወልቂጤ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተመዝግበው ካርድ የወሰዱት ለልማትና ሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መሆኑን የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ለኢትዮጵያ ሰላም፣ ልማትና እድገት ይበጃል ለምንለው ፓርቲ ድምጻችንን ለመስጠት የምርጫ ካርድ እየወሰድን ነው -ወጣቶች በወልቂጤ ከተማ ምርጫ ክልል በሚገኙ 138 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል። ኢዜአ በወልቂጤ ከተማ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች፤ ተመዝግበን ካርድ የወሰድነው ለሀገሪቱ ልማትና ሰላም ቅድሚያ የሚሰጥ የፖለቲካ ፓርቲን ወደ ስልጣን ለማምጣት ነው ብለዋል ። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ አብድልማሊክ ሹሌ ፤ በምርጫው ለመሳተፍና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ይናገራሉ ። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገለጫ በመሆኑም በድምጻቸው ለሀገር ሰላምና እድገት ይበጃል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጅት ማድረጋቸውን ነው የተናገሩት። የከተማው ነዋሪ ወጣት በለጠ ሀብቱ፤ በጠቅላላ ምርጫው ሀገርን ያሳድጋል ብዬ ያመንኩበትን ፓርቲ ለመምረጥ ካርድ ወስጃለሁ ነው ያለው። በተለይ የወጣቶች ስብእና ግንባታ ላይ ትኩረት የሚሰጥ፣ የስራ አጥነት ችግርን የሚፈታና አማራጭ የልማት ፖሊሲን ይዞ የሚቀርብ የፖለቲካ ፖርቲን ለመምረጥ መዘጋጀቱን አመላክቷል። ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በሀገራዊ ምርጫው ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን የገለፁት ደግሞ የከተማው ነዋሪ ወይዘሮ አሰለፈች ይርጉ ናቸው። የመምረጥና መመረጥ መብት በሕገ-መንግስቱ ለዜጎች የተሰጠ ዴሞክራሲያዊ መብት ነው ያሉት ወይዘሮ አሰለፈች ሀገርን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ያሻግራል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወልቂጤ ምርጫ ክልል ስራ አስፈፃሚ አቶ ተገኑ ደመቀ፤ በምርጫ ክልሉ በሚገኙ 138 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። በሁሉም ጣቢያዎች መራጮች ካርድ የሚወስዱት በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዳስታወቀው የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም የሚካሄድ ሲሆን ለዚሁ የሚሆኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።
ማህበራዊ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጉብኝት ተመልሰው በቀጥታ ወደ አርባምንጭ አቀኑ
Mar 14, 2026 26
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጉብኝት ተመልሰው በቀጥታ ወደ አርባምንጭ ማቅናታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በአርባ ምንጭ ዙሪያ እና በመላው ጋሞ ዞን በደረሰው አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ሐዘናቸውን ለመግለጽ እና የሚከናወኑ የድጋፍ ስራዎችን እንደሚገመግሙም ገልጿል። ለቀናት የዘለቀው ከባድ ዝናብን ተከትሎ በአካባቢው የተከሰተው ጎርፍ፤ የመሬት መንሸራተት አደጋ የዜጎቻችንን ህይወት ቀጥፏል፣ በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል ነው ያለው ጽህፈት ቤቱ በመልዕክቱ። ከመጠን በላይ የሞላው የኩልፎ ወንዝም መንደሮችን፣ ቤቶችን፣ የእርሻ ስፍራዎችን፣ የአካባቢ መሠረተ ልማትን ማውደሙን አስታውቋል። ማኅበረሰቡ በከባድ ሀዘን በሚገኝበት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የነፍስ አድን ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል ከተጎጂ ቤተሰቦች ጎን መቆም ይገባናል ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
ተመራቂዎች በመልካም ስነምገባርና በሃላፊነት ስሜት ህዝባቸውን ማገለግል ይጠበቅባቸዋል - ዶክተር ደረጀ ዱጉማ
Mar 14, 2026 18
ነቀምቴ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ተመራቂዎች በላቀ ሥነ-ምግባርና በኃላፊነት ስሜት ሕዝባቸውን ሊያገለግሉ እንደሚገባ የጤና ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ገለጹ። ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 792 ተማሪዎችን ዛሬ በደመቀ ሁኔታ አስመርቋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በበየነ-መረብ መልእክታቸውን ያስተላለፉት የጤና ሚኒስትር ደኤታው ዶክተር ደረጄ፣ ተመራቂዎች የቀሰሙትን ዕውቀት ከዘመኑ ጋር በማዛመድ ለሀገሪቱ የእድገት ጉዞ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይ የጤና ዘርፍ ተመራቂዎች፤ ሙያው ከፍተኛ ሰብአዊነትን የሚጠይቅ መሆኑን ጠቅሰው፣ የእናቶችንና የሕጻናትን ሕይወት የመታደግ ከባድ አደራ በላቀ ሥነ-ምግባርና በኃላፊነት ስሜት እንዲወጡ አስገንዝበዋል። የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ተስፋዬ ለማ(ዶ/ር) እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው በነቀምቴ፣ በሻምቡ እና በጊምቢ ካምፓሶቹ ብቁና የተማረ የሰው ኃይል በማፍራት በኩል ያለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት እየተወጣ ነው። ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ባገኙት ትምህርትና ልምድ ሕብረተሰባቸውን ለማገልገል ቆርጠው መነሳት ይገባቸዋል ብለዋል። የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ መሰረት ኃይሉ በበኩላቸው፤ ውጤቱ የቤተሰብና የመላው ማኅበረሰብ ድካም መሆኑን ገልጸዋል። በዕለቱ በሕክምና ትምህርት ክፍል 3 ነጥብ 5 ውጤት ያስመዘገበችው ዶክተር ሎዛ መድኃኒቴ እንደተናገረችው፣ በዩኒቨርሲቲው በቀሰመችው እውቀት ሴቶችና ሕጻናትን በተሻለ ሁኔታ ለማገልገል ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች። ሌላው 3 ነጥብ 87 ውጤት በማምጣት የዋንጫና የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኖ የተመረቀው ተማሪ ሳሙኤል ኃይሌ፤ ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀሙ ለውጤት መብቃቱን በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ባገኘው ልምድና ትምህርት ማኅበረሰቡን በትጋት ለማገልገል መዘጋጀቱን ተናግሯል። ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ካስመረቃቸው መካከል በመጀመሪያ ዲግሪ 661፣ በሁለተኛ ዲግሪ 125 እና የዶክትሬት ዲግሪ PhD) 6 ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ2 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ
Mar 14, 2026 31
አርባ ምንጭ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ2 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሃዲ፤ በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች የማገዝና የመደገፍ ስራ የሁሉም ሃላፊነት መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የ2 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታውቀዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ(ዶ/ር)፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል። ለወገን ደራሽ ወገን በመሆኑ ከህዝቡ ጎን በመሆን ድጋፍ እያደረጉ ላሉ ተቋማትና ግለሰቦች የላቀ ምስጋና አለን ብለዋል።
ምሩቃን በትምህርት ቆይታቸው በቀሰሙት እውቀትና ክህሎት ሀገርና ህዝብን በቅንነት ማገልገል አለባቸው
Mar 14, 2026 42
ሚዛን አማን፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ ምሩቃን በትምህርት ቆይታቸው በቀሰሙት እውቀትና ክህሎት ሀገርና ህዝብን በቅንነት በማገልገል የተጀመረውን ሀገራዊ የእድገት ጉዞ ሊያፋጥኑ እንደሚገባ ተመለከተ። ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 404 ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል። በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ ፍቅሬ አማን መመረቅ አዲስ የሕይወት ምዕራፍ መከፈትና ለሀገር ግንባታ የዜግነት ኃላፊነት መወጣት ጅማሮ ነው ብለዋል። ተመራቂዎች በቀጣይ ወደ ስራው ዓለም ሲገቡ ሀገርና ህዝብን በታማኝነትና በቅንነት በማገልገል ሙያዊ ግዴታቸውን በታማኝነት ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ለዚህም በትምህርት ቆይታቸው በቀሰሙት እውቀትና ክህሎት መሠረት ሥነ ምግባር የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት ሀገራዊ የለውጥና የዕድገት ጉዞን ማጠናከር እንዳለባቸው ገልጸዋል። በተለይ የጤና ተመራቂዎች ሀገራችን በምትከተለው በሽታን ቀድሞ የመከላከልና አክሞ የማዳን ሥርዓት ላይ ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ በአጽንኦት ተናግረዋል። የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዋቆ ገዳ(ዶ/ር) በበኩላቸው ተመራቂዎች የነገ የማኅበረሰቡ ተስፋ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያካበቱትን ዕውቀትና ክህሎት በቀጣይ ወደ ተግባር በመቀየር ሀገራዊ የለውጥና የዕድገት ጉዞ ላይ ሚናቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ዩኒቨርሲቲው ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመረቃቸው 21 የሜዲካል ዶክተሬት ዲግሪ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ የመውጫ ፈተና በማምጣት የተመረቁ መሆናቸውንም አመልክተዋል። ከተመራቂዎቹ መካከል ዶክተር እፀገነት አያለው 3 ነጥብ 68 በማምጣት በማዕረግ የተመረቀች ሲሆን ትኩረት ሰጥቶ በመማር ከድካም በኋላ የተሻለ ውጤት ማስመዝገቧን ተናግራለች። ስትመረቅ ቃል በገባችው መሠረት ያስተማራትን ማኅበረሰብ በቅንነት ለማገልገል መዘጋጀቷን ገልጻለች። ከፋርማሲ ትምህርት ክፍል በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀው መሐመድ ሐሰን በበኩሉ ሙያዊ ኃላፊነቴን በብቃት ለመወጣት ተዘጋጅቻለሁ ብሏል። መማራችን ትርጉም እንዲኖረው ጤናማ ማኅበረሰብ በመፍጠር ለሀገር ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅብናል ነው ያለው።
ኢኮኖሚ
በሸገር ከተማ ባለፉት ስምንት ወራት 25 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ገቢ ተሰበሰበ
Mar 14, 2026 41
ሸገር፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ ግብርን በቴክኖሎጂ ታግዞ በመሰብሰብና የተሻሻሉ የታክስ ህጎችን በመተግበር ባለፉት ስምንት ወራት 25 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የከተማው ገቢዎች ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የሸገር ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ መልካሙ አምባው ለኢዜአ እንደተናገሩት በከተማው የሚሰበሰብ ገቢን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ነው። ሸገር ከተማ ከመቋቋሙ በፊት ሲሰበሰብ የነበረው ገቢ ከ5 ቢለየን ብር በታች እንደነበርና የከተማው መቋቋምን ተከትሎ የገቢው መጠን እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት ከከተማው 24 በሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታውሰው በተያዘው ዓመትም 39 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱንና ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ 25 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን አስታውቀዋል። ገቢው ከማዘጋጃ ቤታዊ፣ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች የተሰበሰበ መሆኑን ጠቁመው፣ ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለውም ተናግረዋል። የግብር አሰባሰብ ሥራው በቴክኖሎጂ መደገፉ፣ የተሻሻሉ የታክስ ህጎች ተግባራዊ መደረጋቸውና የአገልግሎት አሰጣጡ መዘመኑ ዘንድሮ ከፍተኛ ገቢ እንዲሰበሰብ አስችሏል ብለዋል። የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ ላይ የተሰጠው ትኩረት፣ የግብር ከፋዮች ቁጥር መጨመርና የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ማደግ ለገቢው መጨመር ከፍተኛ እገዛ አድርጓል ነው ያሉት። በዘርፉ ህገ-ውጥ ተግባራትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በተደረገ እንቅስቃሴ ለሸጡት እቃ ደረሰኝ ሳይቆርጡ የተገኙ 59 ግብር ከፋይ ነጋዴዎች በገንዘብ መቀጣታቸውን አንስተዋል። ህግ ተላልፈው በተገኙ 33 የተቋሙ ሠራተኞች ላይም አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ጠቁመው ተግባሩ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን በመኸሩ ከ52ሺህ 900 ቶን በላይ የቡና ምርት ተገኝቷል
Mar 14, 2026 47
ጋምቤላ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን በመኸሩ ከ52ሺህ 900 ቶን በላይ የቡና ምርት መገኘቱን የዞኑ የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት መምሪያ አስታወቀ። በዞኑ ከተመረተው ቡና ከ42ሺህ 624 ቶን በላይ የታጠበና ቅሽር የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገቢያ ለማቅርብ እየተሰራ እንደሚገኝም መምሪያው ገልጿል። በመምሪያው የቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ልማትና ግብይት ቡድን መሪ ሲሳይ በላይነህ፤ በክልሉ ማጃንግ ዞን በዘንድሮው መኸር 52ሺህ 962 ቶን የቡና ምርት መገኘቱን ገልጸዋል።። በዞኑ በሚገኙ የጎደሬና መንገሺ ወረዳዎች በአርሶ አደሩና በባለሃብቶች ከለማው 68ሺህ 637 ሄክታር የቡና ተክል የተገኘ ምርት መሆኑንም ተናግረዋል። በዞኑ በዘንድሮው የምርት ዘመን የተገኘው የቡና ምርት ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ17ሺህ 186 ቶን ብልጫ ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ለተገኘው ውጤትም በዞኑ የተስተካከል የዝናብ ስርጭትና የአየር ፀባይ በመኖሩና የተጠናከረ የቡና ተክልና እንክብካቤ ስራዎች መከናወናቸው እንዲሁም አርሶ አደሩ ከቡና ልማት የሚያገኘው ጥቅም እያደገ በመምጣቱ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ መሆኑንም ተናግረዋል።
በጋምቤላ ክልል በመጪው የመኸር ወቅት ከ180 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ለማልማት እየተሰራ ነው
Mar 14, 2026 101
ጋምቤላ፤ መጋቢት 5/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በመጪው የመኸር እርሻ ከ180 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ ማሳ በተለያዩ ሰብሎች ለማልማት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ ስነ- ምህዳርን መሰረት ያደረገ ስራ ለማከናወነ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ ግብዓት ለማቅረብም እየተሰራ መሆኑን ቢሮው ገልጿል። የቢሮው ኃላፊ አቶ አንድሪው ቱት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ እንደ ሀገር የግብርና ትራንስፎርሜሽን እቅዱን ውጤታማ በማድረግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ ስኬት እየተሰራ ነው። በ2018/19 የመኸር እርሻ ከ180 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በማልማት ከ 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሳብ ታቅዶ ወደ ትግበራ ምዕራፍ መገባቱን ተናግረዋል። በመኸር ወቅት ለማልማት የታቀደው መሬት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ፤ በ8 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ ሲሆን በምርት መጠን ደግሞ የ600 ሺህ ኩንታል ልዩነት ያለው መሆኑን አስረድተዋል። በዚሁ ወቅት መካናይዝድ የግብርና ቴክኖሎጂን ፣የምርጥ ዘርና ሌሎች ግብዓቶችን በስፋት በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳዳግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አሁን ላይ በክልሉ ያለውን ወይና ደጋና ቆላማ ስነ-ምህዳር መሰረት ባደረገ መልኩ የምርጥ ዘር አቅርቦትና ስርጭት ለማከናወን የዘር ግዥ ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። በክልሉ በዘንድሮው የመኸር እርሻ የአፈር ማዳበሪያን በስፋት ጥቅም ላይ በማዋል ምርታማነትን ለማሳደግ ሰፊ የንቅናቄ ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የግብርና ሚኒስቴር ብሔራዊ የሥነ-ምኅዳር ደህንነትን በማስጠበቅ ምርታማነትን የሚያሻሽሉ ብሔራዊ ስትራቴጂዎችን ይፋ አደረገ
Mar 14, 2026 80
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ የግብርና ሚኒስቴር ብሔራዊ የሥነ-ምኅዳር ደህንነትን በማስጠበቅ ምርታማነትን የሚያሻሽሉ ብሔራዊ ስትራቴጂዎችን ይፋ አድርጓል። ይፋ የተደረጉት ስትራቴጂዎች የብሔራዊ ጥምር ደን እርሻ ልማትና ብሔራዊ የሥነ-ምህዳር ስትራቴጂዎች ናቸው። በመርሃ ግብሩ የፌዴራልና ክልል ባለድርሻ አካላት፣ የልማት አጋሮች፣ የጥናትና ምርምር ተቋማት የልማት አጋር ድርጅቶች ተወካዮች ተገኝተዋል። በዚሁ ወቅት የግብርና ሚኒስትር ደኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤሊያስ፤ የግብርና ዘርፍ በሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የማይተካ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአፈር ለምነት መቀነስ፣ የአካባቢ መራቆትና የደን ጭፍጨፋ በግብርና ምርታማነት ላይ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የምርታማነት ስልቶች ተፅዕኖን መቋቋም የሚያስችል አስደናቂ ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል። ብሔራዊ የሥነ-ምኅዳር ስትራቴጂውም በአፈር ጤንነት ጥበቃ፣ በውሃ አጠቃቀምና ብዝኅ ህይወት ደኅንነትን በማስጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል። የብሔራዊ የጥምር ደን እርሻ ልማት ስትራቴጂው የደንና የግብርና መልክዓ-ምድራዊ ሥርዓትን በማሻሻል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ጠቅሰዋል። ሁለቱም ብሔራዊ ስትራቴጂዎች የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነትና የመሬት ለምነት በማሻሻል የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አይነተኛ ሚና እንደሚኖራቸው አስረድተዋል። ለብሔራዊ ስትራቴጂዎቹ ውጤታማነት የልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት ትብብር ወሳኝ መሆኑም በመድረኩ ተገልጿል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በአዳማ ከተማ በሦስት ክፍለ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በይፋ ስራ ጀመረ
Mar 14, 2026 46
አዳማ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ሦስት ክፍለ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በይፋ ስራ ጀመረ። የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና ብልሹ አሰራርን ለመቅረፍ ታስቦ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በአዳማ ከተማ በሚገኙ አባገዳ፣ ቦሌ እና ዳቤ ክፍለ ከተሞች በይፋ ስራ ጀምረዋል። በማስጀመሪያ ስነ-ሥርዓቱ የተገኙት የፌዴራል ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ(ዶ/ር) እንዳሉት የማዕከሉ ወደ ስራ መግባት በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበረውን ችግር እየቀረፈ ነው። በአዳማ የተጀመረው ተሞክሮ በፌዴራልና በክልሎችም ለማስፋፋት እንደ ምሳሌ የሚወሰድ በመሆኑ ኮሚሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የመሶብ አገልግሎት መልካም አስተዳደርን ከማስፈን ባለፈ ዜጎች ከመንግሥት የሚፈልጉትን አገልግሎት የሚያገኙበት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰው በአዳማ የተጀመረው ማዕከላቱን የማስፋፋት ስራ የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል። የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፣ በክልሉ በመጀመሪያው ዙር አገልግሎቱ በተጀመረባቸው ከተሞች ከ500 ሺህ በላይ ዜጎች ተጠቃሚ ሆነዋል ብለዋል። አሁን እየተካሄደ በሚገኘው በሁለተኛው ዙር ማዕከላቱን አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ደግሞ አዳማን ጨምሮ በ26 የክልሉ ከተሞች አገልግሎቱ ስራ ጀምሯል ነው ያሉት። አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ፣ የመልካም አስተዳደር ችግርንና እንግልትን ለመቀነስ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። በሦስተኛ ዙር መርሃ ግብር ደግሞ አገልግሎቱን ወደ 60 ከተሞች ለማስፋፋት የታቀደ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ባለበት ቦታ ሆኖ አገልግሎት የሚያገኝበትን ስርዓት ለመዘርጋት ግብ ተቀምጦ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። አዳማ ከተማ አገልግሎቱን ቀድማ በማስፋፋት ለክልሉ ምሳሌ ሆናለች ያሉት አቶ አወሉ የህዝቡን የአገልግሎት እርካታ ለማረጋገጥ ርብርብ እየተደረገ መሆኑ ገልጸዋል። በቀጣይም ዜጎች ካሉበት ሆነው በቀጥታ አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ የሚሰራ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል። የአዳማ ከተማ ከንቲባ ኃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው በከተማ ደረጃ ከ130 በላይ አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል እየተሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። ዛሬ በተመረቁት ሦስት ክፍለ ከተሞች ደግሞ 110 የሚሆኑ አገልግሎቶች ለህዝቡ ክፍት መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም የዜጎችን እርካታ ከመጨመር ባለፈ የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እንዲጨምር ያስችላል ብለዋል።
የፋይዳ የመመዝገብ አቅምን የሚያሳድጉ ሶስት ሺህ አዳዲስ መመዝገቢያ መሳሪያዎች ወደ ሥራ ሊገቡ ነው
Mar 14, 2026 71
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የመመዝገብ አቅምን የሚያሳድጉ ሶስት ሺህ አዳዲስ መመዝገቢያ መሳሪያዎችን (ባዮሜትሪክ ኪቶች) በቅርቡ ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ። እስከ አሁን የፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ ተመዝጋቢዎች ቁጥር 38 ሚሊየን መድረሱም ተገልጿል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሳሚናስ ሰይፉ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰባት ሺህ መመዝገቢያ መሳሪያዎች አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። የምዝገባ ሂደቱን ይበልጥ ለማቀላጠፍም ተጨማሪ ሶስት ሺህ የባዮሜትሪክስ ኪቶች ተገዝተው ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከመካከለኛው ሲስተም ጋር የማናበብ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። እነዚህ መሳሪያዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገቡ የምዝገባ አቅምን እንደሚያሳድጉ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት በሳምንት እስከ አንድ ሚሊየን ዜጎችን መመዝገብ የሚያስችል አቅም መፈጠሩንም አክለዋል። እስከአሁን ባለው ሂደት የፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ ተመዝጋቢዎች ቁጥር 38 ሚሊየን መድረሱን አስታውቀዋል፡፡ ዜጎች ለምዝገባ በሚመጡበት ወቅት በጣም ባጠረ ጊዜ የፋይዳ መለያ ቁጥራቸው በእጅ ስልካቸው እንዲደርሳቸው እየተደረገ ያለው ጥረት ውጤታማ መሆኑን ጨምረው ጠቅሰዋል። ምዝገባው በስፋት ተደራሽ እንዲሆን ከባንኮች፣ በኢትዮ-ቴሌኮም ቅርንጫፎች፣ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት እንዲሁም ከሌሎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የዲጂታል ሥርዓቱን ከተለያዩ ተቋማት ጋር የማስተሳሰር ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰው፤ ከባንኮች፣ ከወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና ከትምህርት ተቋማት ጋር የማስተሳሰር ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በተለይም ህጻናት በትምህርትና በጤና የተሳለጠ አገልግሎት እንዲያገኙ የፋይዳ መታወቂያ እንዲመዘገቡ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ፋይዳን ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ያስገቡ ተቋማት አገልግሎታቸውን ማዘመን መቻላቸውን የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ በፋይናንስ ተቋማት ላይ የሚስተዋሉ የማጭበርበር ሙከራዎችን በመከላከል በኩል ከፍተኛ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ በተጨማሪም የባንክ ተጠቃሚዎች በፋይዳ አማካኝነት የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና ተቋማት የደንበኞቻቸውን ማንነት በአስተማማኝ ሁኔታ በማረጋገጥ አገልግሎታቸውን እንዲያዘምኑ ማስቻሉንም ገልጸዋል፡፡ ከፋይዳ ዋና ዋና ዓላማዎችና ጥቅሞች መካከል ዲጂታል ኢኮኖሚን መገንባት፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ ደህንነትና አመኔታ፣ የፋይናንስ አካታችነት እና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በክልሉ የዲጂታል 2025 ምርጥ ተሞክሮን በማስፋት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተግባራዊ እየተደረገ ነው
Mar 13, 2026 86
ባህር ዳር ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የዲጂታል 2025 ምርጥ ተሞክሮን በማስፋት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በተሻለ መልኩ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ገለፀ። የዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ እውን እንዲሆን የዜጎችን ክህሎትና እውቀት ማሳደግ ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ምክትል ቢሮ ኃላፊው የቻለ ይግዛው እንዳሉት፤ በክልሉ በ2025 ዲጂታል ኢትዮጵያ የተገኘውን ምርጥ ተሞክሮ በማስፋት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተግባራዊ እየተደረገ ነው። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ተግባራዊ መደረጉም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አሰራራቸውን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የህዝብ ቅሬታን መፍታት እንዳስቻላቸው ነው ያረጋገጡት። ተሞክሮው በቀጣይ አምስት ዓመታት ለሚደረግ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መሳለጥና ማደግ የጎላ አበርክቶ እንደሚኖረው ገልፀዋል። በተጨማሪም ከአድሎ የፀዳ አሰራርን እውን በማድረግ የተጠቃሚውን እርካታ ከፍ የሚያደርግ መሆኑንም አስረድተዋል። በክልሉ በርካታ ተቋማት አሰራራቸውን ዲጂታላይዝ ማድረግ መቻላቸውን ጠቅሰው፤ ይህ የዲጂታላይዜሽን ትራንስፎርሜሽን ትግበራ የተሻለ ውጤት ታይቶበታል ብለዋል። በተለይም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ትግበራ ሰፊ የህዝብ ቅሬታዎችን በአጭር ጊዜ ለመፍታት ያስቻለ እንደሆነ ገልፀዋል። እንዲሁም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በቴክኖሎጂ ታግዞ እየተከናወነ ያለና የተለያዩ አገልግሎቶችን እያዘመነ መሆኑን አብራርተዋል። ዘመኑ ቴክኖሎጂን አብዝቶ መጠቀምን የሚጠይቅና ለዚሁ የሚሆን ምህዳር መፍጠር የግድ በመሆኑ በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት እመርታዊ ለውጥ እየታየ ነው ብለዋል። በቀጣይም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትግበራን በሁለንተናዊ መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋልና እንደ ሃገር የሚጠበቀውን ውጤት ለማስመዝገብ በጋራ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ አመልክተዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ እውን እንዲሆን የዜጎችን ክህሎትና እውቀት ማሳደግ ላይ በትኩረት መስራት ይገባል
Mar 13, 2026 138
ጭሮ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ እውን እንዲሆን ዜጎች በዘርፉ ያላቸውን ክህሎትና እውቀት ማሳደግ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ሀገር በቀል ክህሎትን በማጎልበት የዜጎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ነው ስትራቴጂው የዲጂታል መሰረተ ልማት ዝርጋታን፣ የዲጂታል መታወቂያ ተደራሽነትን፣ የዲጂታል ፋይናንስ መጠናከርን እና ዲጂታል የመንግስት አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረግን ዓላማ አድርጎ እየተተገበረ ይገኛል። የዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ስኬታማ ሊሆን የሚችለውም ዘርፉን በአግባቡ የተገነዘበ፣ በክህሎት እና በእውቀት የጎለበተ ዜጋ ሲገነባ መሆኑም ተመልክቷል። ኢዜአ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር ቆይታ ያደረገ ሲሆን፤ ምሁራኑ የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት የመንግስት አገልግሎቶች ግልጽ፣ ፈጣን እና ቀልጣፋ እንዲሆኑ የጎላ ፋይዳ እንዳለው አመልክተዋል። ከዩኒቨርሲቲው ምሁራን መካከል አቶ ፈቃዱ ወርቁ እንደገለጹት፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ የአገልግሎት አሰጣጥን ከማዘመን ባለፈ ዘመናዊ ከተሞችን በመፍጠር የዜጎችን አኗኗር ያቃልላል። ዘርፉ ለሀገር እድገት ከሚኖረው አስተዋጽኦ መካከል በቴክኖሎጂው ዘርፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን መሳብ እንዲሁም የክፍያ እና የፋይናንስ ዘርፉን ማዘመን ዋና ዋናዎቹ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም የዘርፉን ፋይዳ በአግባቡ ለመጠቀም በዲጂታል ቴክኖሎጂ በቂ ክህሎት እና እውቀት ያላቸው ዜጎችን ማፍራት እንደሚገባ አሳስበዋል። ሌላኛው የዩኒቨርሲቲው ምሁር አቶ ደርብ ገረመው በበኩላቸው፤ በተለይም የ2030 ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ የህዝብ መገልገያ መሰረተ ልማቶችን በማስተሳሰር የዜጎችን ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጥ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት ስራ ላይ የዋለው ዲጂታል መታወቂያ እና የመንግስት ተቋማት ወደ ዲጂታል አሰራር መሸጋገራቸው የዘርፉ ትልቅ እመርታ መሆኑን አንስተዋል። የተጀመረው የዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ግቡን እንዲመታ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት በእውቀት እና በክህሎት ግንባታ ላይ ማተኮር እንዳለባቸውም አክለዋል። በ"ዲጂታል 2025" ስትራቴጂ የተመዘገቡ ስኬቶች ለ2030 ስትራቴጂ መሳካት ጠንካራ መሰረት እንደሚሆኑ የገለጹት ደግሞ አቶ ኢስማኤል ሁሴን ናቸው። በተለይም በፋይናንስ ዝውውር እና በግብይት ስርዓቱ ላይ የታዩ አዎንታዊ ለውጦች፣ እንዲሁም የከተማ ይዞታን በዲጂታል መለያ በማደራጀት ደህንነቱ የተጠበቀ ዳታ መገንባት መቻሉን እንደ ምሳሌ አንስተዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ዘመናዊና ፈጣን አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለመስጠት ምቹ መደላድል እየፈጠረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለቀጣይነቱም የክህሎት እና የእውቀት ግንባታ መጠናከር እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
ስፖርት
ለ"ፊቼ ጫምባላላ" በዓል የሚካሄደው ስፖርታዊ ውድድር በዓሉንና ባህላዊ እሴቶቹን ለማስተዋወቅ እያገዘ ነው
Mar 14, 2026 58
ሀዋሳ፤ መጋቢት 5/2018 (ኢዜአ)፡-የሲዳማ ዘመን መለወጫ "ፊቼ ጫምባላላ"ን በማስመልከት በየዓመቱ የሚካሄደው ስፖርታዊ ውድድር በዓሉንና ባህላዊ እሴቶቹን ለማስተዋወቅና ለማጠናከር እያገዘ መሆኑ ተገለጸ። ለ"ፊቼ ጫምባላላ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ቃል ዛሬ በሀዋሳ ከተማ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ተካሂዷል፡፡ በመርሀግብሩ መሰረትም በወንዶች የ10 ሺህ ሜትር፤ በሴቶች ደግሞ የ5 ሺህ ሜትርና የሕፃናት ውድድሮች ተካሂደዋል፡፡ በውድድሩ ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶማርሶ ዶና በዓሉን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ የሚካሄደው ውድድር የፊቼ ጫምባላላን በዓል ከማድመቅ ባለፈ በውስጡ ያሉትን የአብሮነትና የሠላም እሴቶች ለማስተዋወቅና ለማጠናከር እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። በዛሬው ስፖርታዊ ውድድርም ከክልሉና ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ አንጋፋና አዳዲስ አትሌቶች መሳተፋቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ይህም አዳዲሶቹ ከነባሮቹ ልምድ እንዲቀስሙ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የአካባቢውን አትሌቲክስ ይበልጥ ለማነቃቃት ጠቃሚ መሆኑን አስረድተዋል። ውድድሩን ያዘጋጀው የ“ብራይት አፍሪካ ራን” መስራችና ሥራ አስኪያጅ ካሳሁን ካቢሶ በበኩላቸው በዓሉን ምክንያት በማድረግ ውድድሩ ዘንድሮ ለአራተኛ ጊዜ መካሄዱን ተናግረዋል። በቀጣይ ወደ ፕሮፌሽናል ውድድር እያደገ እንደሚሄድ ጠቁመው፣ ውድድሩ የ"ፊቼ ጫምባላላ" በዓልን ለዓለም በማሳየት ረገድ ጉልህ ድርሻ እንዳለውና ዘንድሮም በተሳካ ድምቀት መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ በሁለቱም ርቀት በተካሄዱ ውድድሮች አንደኛ የወጡ አትሌቶች የሜዳልያና የ30 ሺህ ብር ሽልማት ሲያገኙ እስከ 10ኛ ደረጃን የያዙትም የተለያየ መጠን ያለው ገንዘብና የሜዳሊያ ሽልማት እንደተበረከተላቸው ገልጸዋል። በወንዶች 10 ሺህ ሜትር አንደኛ የወጣው አትሌት አብዱልመጂድ አባደላ ውድድሩን ቀዳሚ ሆኖ ማጠናቀቅ በመቻሉ ደስታ እንደተሰማው ተናግሯል፡፡ ውድድሩ ለበዓሉ ድምቀት የራሱን አስተዋጾ ማድረጉን ጠቅሶ፣ በውድድሩ ከተለያዩ አካባቢዎች ከመጡ አትሌቶችና ከሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ጋር መታደሙ ልዩ ስሜት እንደፈጠረለት ተናግሯል፡፡ የሀዋሳ አየርና ጎዳናው ለውድድሩ ምቹ እንደነበር የተናገረችው ደግሞ በሴቶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድር አንደኛ የወጣችው አትሌት እመቤት ሽብሩ ናት፡፡ ውድድሩ ብቃቷን ለመገምገም ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላት ጠቁማ፣ እንዲህ ያሉ ውድድሮች ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራት ሚናቸው የጎላ በመሆኑ መጠናከር አለባቸው ብላለች። በጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የሲዳማ ክልልና የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ አርሰናል ከኤቨርተን ማንችስተር ሲቲ ከዌስትሃም ዩናይትድ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Mar 14, 2026 79
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል። በዕለቱ አምስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ አርሰናል ኤቨርተንን በኤምሬትስ ስታዲየም ያስተናግዳል። አርሰናል በ67 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። ኤቨርተን በ43 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታው አርሰናል የሊጉን መሪነት ለማጠናከር፣ ኤቨርተን ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ የሚያደርጉት ነው። የ42 ዓመቱ አንዲ ማድሊ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ዌስትሃም ዩናይትድ ከማንችስተር ሲቲ ምሽት አምስት ሰዓት ላይ በለንደን ስታዲየም ይጫወታሉ። ዌስትሃም ዩናይትድ በ28 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ማንችስተር ሲቲ በ60 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ዌስትሃም ዩናይትድ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት በሚያደርገው ትግል ሶስት ነጥብ ማግኘት ወሳኝ ነው። ማንችስተር ሲቲ በዋንጫው ፉክክር ለመቆየት ጨዋታውን ማሸነፍ ይጠበቅበታል። የ41 ዓመቱ ማይክል ኦሊቨር የጨዋታው መሐል ዳኛ ናቸው። ቼልሲ ከኒውካስትል ዩናይትድ ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም ይጫወታሉ። የምዕራብ ለንደኑ ቼልሲ በ48 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ኒውካስትል ዩናይትድ በ39 ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቼልሲ የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ውጥኑን ለማስቀጠል፣ ኒውካስትል ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታሉ። በርንሌይ ከቦርንማውዝ እና ሰንደርላንድ ከብራይተን በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ሃዋሳ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Mar 14, 2026 63
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።’ ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሃዋሳ ከተማ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውድድር ዓመቱ እስከ አሁን ባደረጋቸው 23 ጨዋታዎች ስድስቱን ሲያሸንፍ ስምንት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ ዘጠኝ ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 28 ግቦችን ሲያስቆጥር 30 ግቦችን አስተናግዷል። የ2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ27 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ በሊጉ ባከናወናቸው 23 ጨዋታዎች በ11ዱ ድል ሲቀናው በአምስት ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል። በሰባት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 26 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 14 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ሃዋሳ ከተማ በ42 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ሁለቱም ቡድኖች ተከታታይ ድላቸውን ለማስመዝገብ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ሃዋሳ ከተማ ካሸነፈ ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ያደርጋል። በተያያዘም በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አርባምንጭ ከተማ ከኢትዮጵያ መድን ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አርባምንጭ ከተማ በሊጉ ካደረጋቸው 23 ጨዋታዎች መካከል ማሸነፍ የቻለው ሶስት ጊዜ ብቻ ነው። 10 ጊዜ ሲሸነፍ በተመሳሳይ 10 ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። በ23 ጨዋታዎች 16 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 27 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ19 ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን ካደረጋቸው ጨዋታዎች በአምስቱ ድል ሲቀናው ስምንት ጊዜ ተሸንፏል። 10 ጊዜ አቻ ወጥቷል። 17 ግቦችን ሲያስቆጥር በተመሳሳይ 18 ጎሎች ተቆጥረውበታል። መድን በ25 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። አርባምንጭ ከተማ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታል። ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አቻ የወጣው ኢትዮጵያ መድን ማሸነፍ ወደ ድል መንገድ ይመልሰዋል። ኢትዮጵያ ቡና ከአዳማ ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ቡናማዎቹ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀራቸው በ29 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዘዋል። አዳማ ከተማ በ33 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሁለቱም ቡድኖች በ23ኛ ሳምንት ካስተናገዱት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። በሌላኛው መርሐ-ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከድሬዳዋ ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ25 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ድሬዳዋ ከተማ በ28 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። በ23ኛ ሳምንት ወልዋሎ ከመቻል ጋር ያለ ግብ አቻ ሲለያይ ድሬዳዋ ከተማ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ ይጫወታሉ።
ሲዳማ ቡና ምድረ ገነት ሽሬን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
Mar 13, 2026 125
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሲዳማ ቡና ምድረ ገነት ሽሬን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ብርሃኑ በቀለ እና አዲስ ፈራሚው አቤል ያለው ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሲዳማ ቡና ነጥቡን ወደ 45 ከፍ በማድረግ መሪነቱን አጠናክሯል። ከተከታዩ ሃዋሳ ከተማ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ 12ኛ ድሉንም አስመዝግቧል። በአንጻሩ በሊጉ ስምንተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ምድረ ገነት ሽሬ በ27 ነጥብ 14ተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች አላሸነፈም። በዝውውር መስኮቱ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ሲዳማ ቡና ያመራው አቤል ያለው በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 10 ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መምራት ጀምሯል። ለሲዳማ ቡና በሁለት ጨዋታዎች ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ባህርዳር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አንተነህ ተፈራ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥሯል። ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ባህር ዳር ከተማ በ31 ነጥብ ደረጃውን ከ10ኛ ወደ 8ኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ ስድስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ25 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት ስምንት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ዛሬ ቀን ላይ በተደረጉ የ24ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች ሸገር ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ፋሲል ከነማ እና መቻል ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
አካባቢ ጥበቃ
የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስኬት በምሳሌነት የሚወሰድ ነው
Mar 14, 2026 26
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስኬት በምሳሌነት የሚወሰድ የልማት አጀንዳ መሆኑን በኢትዮጵያ የሕንድ አምባሳደር አኒል ኩመር ራይ ገለጹ። አምባሳደር አኒል ኩመር ራይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በርካታ ችግኞችን በመትከል የካርቦን ልቀትን መቀነስ የሚያስችል ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል። ከብክለት ነፃ የሆኑ የትራንስፖርት አማራጮችን በማስፋት በኩልም ለአየር ንብረት ተፅዕኖ የማይበገር አረንጓዴ የኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ወሳኝ እርምጃ እየወሰደች እንደምተገኝም አንስተዋል። የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስኬት በምሳሌነት የሚወሰድ የልማት አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የኢኮኖሚ ሥርዓት ግንባታም ለሌሎች የአፍሪካ እና የዓለም ሀገራት ተሞክሮ የሚወሰድበት መሆኑን ገልጸዋል። ሕንድም ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት በምታደርገው ጥረት ትብብሯን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። በቅርቡ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ የፕላስቲክ መያዣዎች ላይ የእግድ ውሳኔ መተላለፉ ለአካባቢ ደኅንነትና ሥነ-ምኅዳር ጥበቃ ጉልህ ፋይዳ ያለው ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም ሕንድ በአካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ሥርዓት ያላትን ልምድና ተሞክሮ በማጋራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸዋል።
አዋጁ እንደ ሀገር የተጀመረውን የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ከግብ ለማድረስ ያግዛል
Mar 13, 2026 194
አሶሳ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦የተሻሻለው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ አዋጅ እንደ ሀገር የተጀመረውን የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ከግብ ለማድረስ እንደሚያግዝ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አካባቢና ደን ጥበቃ እና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ። በክልሉ ህብረተሰቡ በፕላስቲክ ከረጢት ምትክ አማራጭ ምርቶችን በስፋት እንዲጠቀም እየተደረገ መሆኑም ተመላክቷል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ፣ የወንዝ ዳርቻ፣ የከተማና ገጠር ኮሪደር ልማት ስኬቶች ጤናማ የአካባቢ ሥነ-ምኅዳር መፍጠር አስችለዋል የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሉቅማን አብዱልቃድር እንዳስታወቁት፤ የተሻሻለውን የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ አዋጅ በክልሉ ተግባራዊ ለማድረግ በተለያዩ መድረኮች ህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲኖረው ተደርጓል። በዚህም በፕላስቲክ ምርት ንግድ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች አማራጭ ምርቶችን ማምረት እንዲጀምሩ በተግባር የታገዘ የሙያ ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። በአሁኑ ሰዓት የተወሰኑ ግለሰቦች ተኪ ምርቶችን ማዘጋጀት መጀመራቸውን ጠቁመው፥ በዘርፉ ላይ ለሚሰማሩ አካላት አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ ተናግረዋል። የፕላስቲክ ከረጢቶች ለአካባቢ ብክለት መንስኤ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ሉቅማን አዋጁ እንደ ሀገር የተጀመረውን የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ከግብ ለማድረስ ያግዛል ብለዋል። አዋጁን ተከትሎ የፕላስቲክ ከረጢቶችን የሚተኩ ምርቶች ላይ የተሰማራችው ወጣት ጅራቱ ሰንበቶ በበኩሏ፤ አዋጁን ተግባራዊ ለማድረግ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ ይገባል ብላለች። በቅርቡ ወደ ስራ መግባቷን ገልጻ አዲስ አበባ በመሄድ ሙያዊ ስልጠና መውሰዷን ተናግራለች። በአሁኑ ሰዓት ሌሎች በዘርፉ የሚሰማሩ የስራ ዕድል ተጠቃሚዎችን ለማሰልጠን ፍላጎት እንዳላት ገልጻ ጎን ለጎንም ለንግድ ተቋማት የወረቀት ከረጢቶችን በማዘጋጀት የማስተዋወቅ ስራ እያከናወነች መሆኑን ተናግራለች። አዋጁን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ በማድረግ የፕላስቲክ ከረጢቶች የሚያደርሱትን የአካባቢ ብክለትና በህብረተሰቡ ላይ የሚያስከትሉትን የጤና ጠንቅ መከላከል እንደሚገባም ነው የገለጸችው።
በበልግ ዝናብ ተጠቃሚና ሰብል አብቃይ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚኖረው የዝናብ ሁኔታ ለግብርና ስራ አዎንታዊ ሚና ይኖረዋል
Mar 12, 2026 108
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2018(ኢዜአ)፦ በቀጣዮቹ አስር ቀናት በበልግ ዝናብ ተጠቃሚና ሰብል አብቃይ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚኖረው የዝናብ ሁኔታ ለግብርና ስራ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ኢንስቲትዩቱ ከመጋቢት 2 እስከ መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ.ም የሚኖረውን የአየር ሁኔታ አዝማሚ አስመልክቶ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በቀጣዮቹ አስር ቀናት ለዝናብ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩ የሚቲዎሮሎጂ ገፅታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። ኢትዮጵያ የሰርኩላር ኢኮኖሚን የልማት እቅዷ አካል በማድረግ በአካባቢ ጥበቃ ለአፍሪካ አርዓያ የሚሆን ተግባር እያከናወነች ትገኛለች በልግ ዋነኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት በደቡብ እና በደቡብ ምስራቅ፣ የስምጥ ሸለቆና አጎራባች አካባቢዎች፣ የመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች እንዲሁም በደቡብ ምዕራብ ላይ የተሻለ ገፅታ እንደሚኖራቸው ይጠበቃል። በዚህም በደቡብ፣ መካከለኛው፣ ምስራቅና እና ሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ይጠበቃል። እነዚህ አካባቢዎች በጥቂት ስፍራዎቻቸው ላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የትንበያ መረጃዎች ያመላክታሉ። በዚህም መሰረት ወላይታ፣ ጎፋ፣ ጌዴዮ፣ ጋሞ፣ ባስኬቶ፣ አሪ፣ ኮንሶ፣ ቡርጂ፣ አሌ፣ ጋርዱላ፣ ኮሬ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም ሁሉም የሲዳማ ክልል ዞኖች ከመካከለኛ እስከ ከባድ የዝናብ መጠን ያገኛሉ ብሏል ኢንስቲትዩቱ። ይህ የዝናብ መጠን በቂ የአፈር እርጥበት እንዲኖር፣ የሰብሎች የውሃ ፍላጎት መሟላት፣ ለቋሚ ተክሎች እድገትና የግጦሽ ሳርና የመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሻሻል እንዲኖር በማድረግ ለግብርና ሥራ አዎንታዊ ሚና እንዳለው ጠቅሷል። የአፈር መሸርሸር፣ በሰብል ማሳ ላይ ውሃ መተኛት፣ የሰብል በሽታና ተባይ እንዲሁም የአረም መከሰት ሊያስከትል እንደሚችልም አስጠንቅቋል። ስለሆነም የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችን መስራት፣ የሰብል በሽታንና አረም እንዳይስፋፋ መከላከል፣ የሰብል ማሳዎችን በቅርበት መከታተልና የአየር ጠባይ ትንበያና ምክረ ሃሳቦችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል። በመሆኑም የአየር ሁኔታው አስተዋፅኦ በላቀ ሁኔታ ለመጠቀምና ሊከሰት የሚችለውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለመቀነስ የሚቲዎሮሎጂ ምክረ ሀሳቦችን ከወዲሁ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አስረድቷል። በሌላ በኩል በጋምቤላ፣ በአፋር፣ በሶማሌ፣ በቤንሻንጉል-ጉሙዝና በምዕራብ አማራ አካባቢዎች ቀን ላይ ከፍተኛ የሙቀት መጠን እንዲሁም ሌሊት ላይ ወበቅ እንደሚጠበቅ ገልጿል።
በጉጂ ዞን ድርቅንና የአካባቢ መራቆትን በዘላቂነት ለመቋቋም የሚያስችሉ ችግኞች እየተዘጋጁ ነው
Mar 11, 2026 93
ነጌሌ ቦረና ፤ መጋቢት 2/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በዘንድሮው ዓመት ለሚካሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ድርቅንና የአካባቢ መራቆትን በዘላቂነት ለመቋቋም የሚያስችሉ ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በኦሮሚያ ክልል የተሻሻሉና የአካባቢን ስነ-ምህዳር ታሳቢ ያደረጉ የቡና ችግኞች ይተከላሉ በጽህፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ቡድን መሪ አቶ ወንዶ ሸርቦቴ ለኢዜአ እንዳሉት፤በዘንድሮ የክረምት ወቅት ለሚካሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ድርቅንና የአካባቢ መራቆትን ለመቋቋም የሚያስችሉ ችግኞች እየተዘጋጁ ነው። የችግኝ ዝግጅቱ በዞኑ ባሉ ከ170 በላይ ችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች እየተካሔደ ሲሆን እስካሁን ባለው ሒደት 89 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን ለማዘጋጀት መቻሉን አስታውቀዋል። ይህም በየዓመቱ የሚከሰተውን ድርቅና የአካባቢ መራቆት ችግርን በዘላቂነት ለመቋቋም እንደሚያስችል ታምኖበታል ነው ያሉት። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካል የሆነው የችግኝ ዝግጅቱ የጉጂ ዞንን ደጋ፣ ወይና ደጋና ቆላማ የአየር ንብረት ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አውስተዋል። ለተከላ ከተዘጋጁት የችግኝ ዝርያዎች ውስጥ ጽድ፣ ግራቪሊያ፣ ወይራ፣ ዋንዛ፣ ዝግባና ሌሎችም እንደሚገኙበት ነው ያመለከቱት። እንዲሁም ለከተማ ውበት፣ ለእንስሳት መኖ፣ ለምግብነት የሚውሉና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ሙዝና ግሽጣ ያሉ ፍራፍሬዎችን ያካተተ የችግኝ ዝግጅት መደረጉን አስረድተዋል። ችግኞቹን ለማልማትና ለውጤት ለማብቃት ከሰውና ከእንስሳት የተከለለ ከ21 ሺህ 340 ሄክታር በላይ መሬት መዘጋጀቱን አስረድተዋል። በመጪው ክረምት በሚካሄደው የችግኝ ተከላ ስራ ከ205 ሺህ በላይ ህዝብ ለማሳተፍ የቅስቀሳና የግንዛቤ ማሳደግ ስራ እየተካሄደ እንደሚገኝም አመላክተዋል። በዞኑ ባለፈው ዓመት ከተተከሉት ችግኞች በህዝብ እንክብካቤና ጥበቃ 83 በመቶው መጽደቁን በመስክ ምልከታና ክትትል ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የኢጋድ እና ጃፓን ትብብር መጠናከር ለቀጣናዊ ሰላም የጎላ ሚና አለው
Mar 9, 2026 135
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና ጃፓን በቀጣናው ሰላም ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሠሩ ገለጹ። የኢጋድ ምክትል ዋና ፀሐፊ መሐመድ አብዲ ዋሬ ከጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ዳይሬክተር ሂሮኒሪ ሱዙኪ ጋር በጅቡቲ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በኢጋድ ቀጣና ስላለው የሰላም እና ደኅንነት ሁኔታ ሐሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቀጣይም ትብብራቸውን በይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሠሩ ማረጋገጣቸውን ኢጋድ ሴክሬተሪያት መረጃ ጠቁሟል። ጃፓን ለኢጋድ እና አባል ሀገራት፤ በቀጣናው ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት መረጋገጥ ሥራ ዋና አጋር ሆና መቀጠሏም ተመላክቷል።
ሀገራት የሴቶች መብቶችን የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባቸዋል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Mar 9, 2026 119
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የሴቶች መብቶች እና የሥርዓተ ጾታ እኩልነነት የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን እንዲወስዱ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጥሪ አቀረቡ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። "መብቶች፣ ፍትሕ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሐሳብ ነው። የአፍሪካ ኀብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም፤ ቀኑ የአፍሪካ ሴቶች እና ልጃገረድ ስኬቶችን የምናከብርበት፣ ሴቶችን ማብቃት እና ጥበቃ ላይ የገባናቸውን ቃል ኪዳኖች ዳግም የምናድስበት ነው ብለዋል። ሴቶች በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ከአመራር ሰጪነት እስከ ቴክኒካዊ ቦታዎች ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም አመልክተዋል። የሥርዓተ ጾታ እኩልነት የተቋሙ ሥራ ማዕከል መሆኑንም አስረድተዋል። የአፍሪካ ኅብረትም ቀኑን እያከበረ ሲሆን፤ የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር በአፍሪካ የሴቶችን መብቶች የሚደግፉ ቁልፍ ማዕቀፎችን በዚሁ ወቅት አንስተዋል። ለአብነትም የአፍሪካ ኅብረት የሰው እና ዜጎች መብቶች ቻርተር የሴቶች መብቶች የሕግ ማዕቀፍ፣ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) እና የሴቶችና ልጃገረዶች ጥቃትን ማስቆም ያለመውን የኅብረቱ ን ኮንቬንሽን በማሳያነት ጠቅሰዋል። የኮንቬንሽኑ ወደ ትግበራ መግባት ትልቅ ስኬት እንደሆነ ገልጸው፤ ሀገራት በሕግ አውጪ ምክር ቤት ማዕቀፉን በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲያስገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ሊቀ መንበሩ የሥርዓተ ጾታ እኩልነት እና የልማት የትኩረት መስኮች ቁርኝት እንዳለውም አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የ2026 ትኩረት በሆነው ውኃ እና ንጽህና ጋር በተያያዘ፤ ሀገራት የሴቶችን ጫና የሚያቃልሉ እና ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን እንዲያከናውኑም ጥሪ አቅርበዋል።
በቀጣናው የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው -ኢጋድ
Mar 8, 2026 126
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂን ጨምሮ በቀጣናው የሴቶችን የአመራርና ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው። "መብቶች፣ ፍትህ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሴቶችን ቀን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፏል። ኢጋድ ለሴቶች አመራር ሰጪነት፣ አይበገሬነት እና በቀጣናው ሰላም፣ ብልጽግና እና ለውጥ ለማምጣት እያበረከቱት ላለው አስተዋጽኦ ክብር እና እውቅና እንደሚሰጥ ገልጿል። በኢጋድ ሴቶች በቀጣናው አመራር ሰጪነት ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። የኢጋድ የሰላም፣ ግብርና፣ ዲጂታል ደህንነት፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና መሬት አስተዳደር ፎረሞች እንዲሁም የኢጋድ የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂ ጨምሮ የተለያዩ ኢንሼቲቮች እየተገበረ መሆኑን አመልክቷል። የሴቶች ድምጽ እንዲሰማ እና መሉ ተሳትፏቸው እንዲረጋገጥ የሚያግዙ መድረኮችን መፍጠሩን ነው የኢጋድ ሴክሬተሪያት በመረጃው ያስታወቀው።
ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በሰላምና ደኅንነት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Mar 5, 2026 162
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢጋድ የሰላም እና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ውይይቱን ያደረጉት የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁን (ዶ/ር) በመወከል ነው። ውይይቱ ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም፣ ደኅንነት እና መረጋጋት ላይ ያላቸውን የጋራ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው። ሁለቱ ወገኖች የጋራ የተግባር ምላሽ ለመስጠት እና ስትራቴጂካዊ ትብብራቸውን ለማጎልበት ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 272
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 318
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 315
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 749
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 357
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 460
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1180
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1189
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3669
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2449
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8246
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6732
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 505
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 470
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።