ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ኢንስቲትዩቱ የመኖ እጥረትን ለመፍታት የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ ሊያጠናክር ይገባል
Jan 21, 2026 17
አዳማ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የመኖ እጥረትን ለመፍታትና የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ ሊያጠናክር እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። የቋሚ ኮሚቴው አመራሮችና አባላት በአዳማ ከተማ በሚገኘው የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምርምር ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ አድርገዋል። በዚህ ጊዜ በምክር ቤቱ የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፤ ኢንስቲትዩቱ የህብረተሰቡን ችግር በተጨባጭ መፍታት የሚችሉ ምርምሮች ለማከናወን እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀዋል። ደረቅ ቆሻሻን ወደ እንስሳት መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለመለወጥ የሚያስችል የፈጠራ ቴክኖሎጂ እውን ማድረጉ የዚህ ማሳያ መሆኑን በመጥቀስ። በገጠርም ይሁን በከተማ በዶሮና ዓሳ እርባታ የተሰማሩ ወጣቶችና አርሶ አደሮች መኖን በቀላሉ በቤታቸው እንዲያዘጋጁ ድጋፍ በማድረግ የመኖ እጥረትን ለመፍታት የኢንስቲትዩቱ ሚና ወሳኝ መሆኑንም ነው ያብራሩት። ኢንስቲትዩቱ ጠቃሚ የምርምር ውጤቶችን በማስፋፋት በባዮ ኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ ሚናውን የበለጠ እንዲያጎላም ጠይቀዋል። መኖን በአገር ውስጥ ማምረት የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግ መሆኑን ጠቅሰው፣ ኢንስቲትዩቱ በዚህ ረገድ የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል። የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ ፍሬው ታፈሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ስምንት ወራት ቆሻሻን ወደ ከፍተኛ ፕሮቲን ያለው የእንስሳት መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ የሚቀይር “ነብሳት” የተሰኘ ፕሮጀክት በመቅረፅ ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል። ቴክኖሎጂው ፍራፍሬን ጨምሮ የግብርናና የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶችን በመፍጨትና በማብላላት ወደ መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ የሚቀይር መሆኑን አስረድተዋል። አሁን ላይ በሳምንት 10 ኩንታል የዶሮ መኖ በማምረት በአዳማ ሰርቶ ማሳያና የስልጠና ጣቢያ የዶሮ እርባታ መጀመሩን ገልጸዋል። የዶሮ መኖን ከተረፈ ምርት የማግኘት፣ የማላመድና የማሳደግ ተግባራትን ወደ ተጠቃሚው ለማሸጋገር በሂደት ላይ መሆኑን አመልክተዋል።
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና ሸገር ከተማ አቻ ተለያዩ
Jan 21, 2026 28
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና ሸገር ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሄኖክ አዱኛ በ22ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠራት ግብ ሸገር ከተማ መሪ ሆኗል። ሐዋሳ ከተማ ከነገሌ አርሲ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው ጋናዊው ኮንኮኒ ሀፊዝ በ33ኛው ለወልዋሎ የአቻነቷን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ቡልቻ ሹራ ከሸገር ከተማ፣ ሰመረ ሀፍታይ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥተዋል። ሸገር ከተማ በ16 ነጥብ ደረጃውን ከ17ኛ ወደ 16ኛ ከፍ በማድረግ ከወራጅ ቀጠና ወጥቷል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ13 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሁለቱ ቡድኖች በተመሳሳይ ያለፉትን ሰባት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻሉም።
በጎንደር ከተማ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ለ142 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ ተሰጥቷል
Jan 21, 2026 40
ጎንደር ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ በጎንደር ከተማ በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከ43 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 142 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ገለጸ። በጎንደር ከተማ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ባለሀብቶች፣ ዳያስፖራዎችና ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የኢንቨስትመንት ፎረም ተካሂዷል። በዚሁ ጊዜ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ ግርማይ ልጃለም፤ ፎረሙ ከተማዋ ያላትን የልማት ጸጋዎች ለማስተዋወቅና አዳዲስ ባለሃብቶችን ለመሳብ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በከተማዋ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 142 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል። ፈቃድ የተሰጣቸው ባለሃብቶች በአምራች ኢንዱስትር፣ በግብርናና በአገልግሎት ዘርፍ የሚሰማሩ መሆኑንም ተናግረዋል። እነዚህ ባለሃብቶች ወደ ሥራ ሲገቡ በከተማዋ ለሚገኙ 29 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ በመግለጽ። እስካሁን ባለው ሂደት ለ17 ባለሃብቶች 17 ሄክታር የግንባታ ቦታ መሰጠቱን ጠቅሰው፣ ወደ ግንባታ ለገቡ 22 አምራች ኢንዱስትሪዎች የመብራት፣ የውሃና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መሟላቱን አመልክተዋል። በከተማዋ የተከናወኑ የቱሪዝምና የኮሪደር ልማት ሥራዎች በርካታ ባለሀብቶች መዕዋለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ነው የመምሪያው ኃላፊ የተናገሩት። በመምሪያው የኢንዱስትሪ ልማት ቡድን መሪ ፋሲል ዘውዱ ባቀረቡት የውይይት መነሻ፤ በከተማዋ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች ምቹ ምህዳር ተፈጥሯል ብለዋል። በኢንዱስትሪ መንደር ውስጥ ከ700 ሄክታር በላይ ቦታ መዘጋጀቱን ለአብነት አንስተዋል። የግንባታ ፍቃድ ወስደው ግንባታ ያልጀመሩና ቦታውን አጥረው በቆዩ ባለሃብቶች ላይ አስፈላጊው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አመልክተው፣7 ባለሃብቶች የወሰዱትን መሬት ባለማልማታቸው ወደ መሬት ባንክ ገቢ መደረጉን ተናግረዋል። የፎረሙ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፣ በከተማዋ እየታየ ያለው ሰላምና መረጋጋት ለኢንቨሰትመንት አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ሲሳይ ወንድሙና ዘይኑ መሀመድ ከተማዋ ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆኗን አንስተዋል። ከኢንቨስትመንት ፍቃድ አሰጣጥ ጀምሮ ያለው ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት የባለሀብቶችን ቀልብ የሚስብ ነው ብለዋል።
በወራቤ ከተማ ግንባታው እየተከናወነ ያለው የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ የከተማዋን እድገት እያፋጠነ ነው
Jan 21, 2026 30
ወራቤ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ በወራቤ ከተማ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ግንባታው እየተከናወነ ያለው የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ የከተማዋን እድገት እያፋጠነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሻፊ ሙዜ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማዋ በራስ አቅምና በህብረተሰቡ ተሳትፎ በ1 ቢሊዮን 610 ሚሊዮን ብር 5 ነጥብ 73 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ እየተገነባ ነው። ከከተማ የውስጥ ለውስጥ አስፓልት መንገድ ሥራ ጎን ለጎንም የፍሳሽ ማስወገጃ ትቦ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው። በሁለት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ታቅዶ ወደ ተግባር ከተገባው የመንገድ ስራም ውስጥ 1 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትሩ ለአስፓልት ንጣፍ ዝግጁ መደረጉን ገልጸዋል። የአስፓልቱ ግንባታ ሥራ በከተማው በ1 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እየለማ የሚገኘውን የሶጃት ኢንዱስትሪ መንደርን ጨምሮ ሌሎች አካባቢዎችን እንደሚያገናኝም ተናግረዋል። የአስፓልት መንገድ ግንባታ ሥራውን በታቀደለት ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ በከተማው የቀበሌ 01 ነዋሪ አቶ ጅብሪል አማን ለኢዜአ እንዳሉት፤ በከተማ አስተዳደሩና በህብረተሰቡ ተሳትፎ እየተሰራ ያለው የውስጥ ለውስጥ አስፓልት መንገድ ግንባታ ለከተማው የንግድ ሥራ መነቃቃት ከመፍጠር ባለፈ የትራንስፖርት ፍሰቱን እንደሚያቀላጥፈው ተናግረዋል፡፡ ለአስፓልት መንገዱ ሥራ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ገልፀዋል፡፡ ሌላው የዚሁ ከተማ ነዋሪ አቶ ሸረፈዲን ሹሜ እንደገለጹት፤ ለአንድ አካባቢ ፈጣን እድገት መረጋገጥ የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ማስፋት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው። የከተማው አስተዳደር እያከናወነ ያለው ተግባር በከተማዋ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና የከተማዋን ፈጣን እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝም ተናግረዋል፡፡
የንግድ ስርዓቱን ለማዘመንና የግብይት ማዕከላትን ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቷል
Jan 21, 2026 61
ኮምቦልቻ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ ገበያውን ለማረጋጋት የንግድ ስርዓቱን ለማዘመንና የግብይት ማዕከላትን ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ። በኮምቦልቻ ከተማ በ120 ሚሊየን ብር የተገነባው የገበያ ማዕከል ተመርቋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በተበታተነ መንገድ የሚደረግ ግብይትን በማሰባሰብና የግብይት ስርዓቱን በማዘመን የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት እየተሰራ ነው። በተጨማሪም የግብይት ስፍራዎችን ማልማት፣ ይዞታቸውን ማስከበር እንዲሁም ደረጃቸውን በማሻሻል ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በከተሞች የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ተቋቁመው ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እና በቅናሽ እንዲቀርብ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ዛሬ በኮምቦልቻ ከተማ የተመረቀው የገበያ ማዕከልም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰው ስራው በሌሎች ከተሞችም መስፋት እንዳለበት ጠቁመዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የክልሉን ሰላም ከማጽናት በተጓዳኝ ለሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በተለይ ገበያን በማረጋጋት የኑሮ ውድነቱን ማቃለል እንዲቻል የገበያ ማዕከላትን የማስፋፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢብራሂም መሀመድ(ዶ/ር) ቀደም ሲል ሸማችና አምራቹን የሚያገናኙ የገበያ ማዕከላት በስፋት ባለመኖራቸው የንግድ ስርዓቱ ለህገ ወጥ ተግባራት የተጋለጠ ነበር ብለዋል። ይህን ችግር ለመቅረፍም በተለያዩ አካባቢዎች የገበያ ማዕከላት ተገንብተው ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቁመው በቅርቡ ወደ ሥራ የገባው የደሴ ገበያ ማዕከልም ውጤታማ ሆኖ መቀጠሉን አንስተዋል። ዘንድሮም ክልሉ ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ መድቦ የገበያ ማዕከላትን ለማስፋፋትና ደረጃቸውን ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል። የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መሀመድአሚን የሱፉ በበኩላቸው፣ በማዕከሉ የኢንዱስትሪ እና የግብርና ምርቶች ለሕብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ይቀርባሉ ነው ያሉት። በምርቃቱ የፌዴራል፣ ከክልሎች የተውጣጡ የንግዱ ዘርፍ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ፖለቲካ
ምክር ቤቱ የምርጫ አዋጁን በማሻሻል በቴክኖሎጂ የታገዘ ግልጽና ፍትሐዊ ምርጫ እንዲካሄድ አስቻይ ሁኔታዎችን ፈጥሯል
Jan 21, 2026 88
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ አዋጁን በማሻሻል፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ግልጽ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ምርጫ ማከናወን የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ማድረጉን የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲከናወንና ድምፅ መስጫውም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሆን መወሰኑ ይታወሳል። ቦርዱ ይህንን ታሳቢ በማድረግ ከግብዓት ማሟላት እስከ ሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች የተለያዩ ዝግጅቶችን ማድረጉን አስታውቋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሀገሪቱ ምርጫና ድምጸ-ውሳኔ የሚያካሂድ ገለልተኛ ሕገ-መንግሥታዊ ተቋም ነው። ቦርዱ በሕገ-መንግሥቱ መሠረት 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ በቂ ዝግጅት ማድረጉን በሪፖርቱ ማረጋገጡን ገልጸዋል። ምክር ቤቱ 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊና ተዓማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊ የሕግ ማሻሻያዎች ማድረጉን ጠቁመዋል። በተለይም አዋጅ ቁጥር 1162/2011ን በማሻሻል የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባ እንዲሁም ሌሎች የቦርዱ ሥራዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ እንዲሆኑ አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን አብራርተዋል። የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ምርጫውን በመታዘብና ለመራጮች ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ወሳኝ ሚና እንዳላቸውም ገልጸዋል። መንግሥት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሠረት የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት የሚያሳልጡ ዝግጅቶችን እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በብሔራዊ መግባባት እንዲከናወን ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቀሰው ለምርጫው ስኬታማነት ሁሉም አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን በማረጋገጥ ረገድ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እያስመዘገበች ነው
Jan 20, 2026 148
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የወል ትርክትን በመገንባትና ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ ረገድ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እያስመዘገበች መሆኗን የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ያሏት ፀጋዎች ሁለንተናዊ ዕድገትን ለማምጣት እና ዜጎችን የሚያስተሳስር የጋራ ትርክት ለመገንባት ወሳኝ ናቸው። እነዚህን ፀጋዎች በውል ተገንዝቦ ሀገራዊ ፋይዳ ላለው ተግባር ማዋል ባለመቻሉ እና በሚያስተሳስሩን ጉዳዮች ላይ ትኩረት ባለመደረጉ ሀገራዊ ዕድገት ተገድቦ ቆይቷል ብለዋል። በአንፃሩ አሁን ላይ ተገቢውን ትኩረት ያገኘው የጋራ ትርክት ጉዳይ እነዚህን ማነቆዎች በመፍታት ለሀገር ብልጽግና መሠረት እንደሚሆን አመላክተዋል። የለውጡ መንግሥት አብሮነትን የሚያጎሉ የጋራ ትርክት ግንባታ ላይ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተጽፈው ለንባብ የበቁት የመደመር መጻሕፍት፤ ዜጎች ስለ ሀገራቸው ያላቸውን አረዳድ በማስተካከልና የወል ትርክትን በመቅረጽ ረገድ ትልቅ ሚና አላቸው ብለዋል። በሀገሪቱ በተግባር ዕየታዩ የሚገኙ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶች የዜጎችን አንድነት ከማጠናከር ባለፈ ውስጣዊ ጥንካሬንና ብሔራዊ ኩራትን ማጎልበት የሚችል ዐቅም መፈጠሩንም ተናግረዋል፡፡ ይህም ለትውልድ ቀረጻና ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚውል የጋራ ትርክት የመፍጠር ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ያመላክታል ነው ያሉት። ፈጠራ የታከለበት የመንግሥት ፈጣን አስተሳሳሪ የልማት አካሄድ፤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን በዓለም አቀፍ ደረጃ እንድታስከብር ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው በአጽንኦት አንስተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከናወኑ የብሔራዊ ትርክት ግንባታ ሥራዎች ኢትዮጵያ ውስጣዊ አንድነቷን እንድታጠናክርና ጥቅሞቿን እንድታስከብር ዕድል መፍጠራቸውንም ጠቁመዋል። ይህም ሀገሪቱ ሉዓላዊነቷንና ጥቅሟን በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሀገራዊ የከፍታ ምዕራፍ ላይ መድረሷን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብና የባሕር በር ባለቤትነትን የማረጋገጥ ጥረቶችን በዋነኛ ማሳያነት ጠቅሰዋል። እነዚህም ኢትዮጵያ ያላትን ትልቅ ዐቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያስመሰከሩና ዜጎችን በአንድ የጋራ ዓላማ ሥር ያሰለፉ መሆናቸው ነው የገለጹት። በሕዳሴ ግድብ አማካኝነት ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት በቀጣናዊ የኃይል ትስስር ረገድ ያበረከተችውን ሚና ዓለም እንዲያውቀው አስችሏልም ብለዋል። ፍትሐዊ የባሕር በር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ታሪካዊ ግስጋሴም፣ የጋራ ትርክት መገንባት ዜጎችን በአንድ ልብ ለማሰለፍ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
Jan 20, 2026 135
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 52ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ምክር ቤቱ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች እንደሚከተለው ቀርቧል፦ 52ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች ጥር 12 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 52ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ በሥራ ላይ ያለው የጉምሩክ አዋጅ ለበርካታ ዓመታት ያገለገለ በመሆኑ፣ የአዋጁን ድንጋጌዎች ዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ከደረሰበት የዕድገት ደረጃ ጋር ለማጣጣም፣ በአገራችን እያደገ የመጣውን የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ለመደገፍ፣ እንዲሁም ሕጋዊ ንግድንና ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት ይቻል ዘንድ የማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል አዋጁ ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምፅ ወስኗል፡፡ 2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው ለኢንቨስትመንት ስለሚሰጥ የታክስና ቀረጥ ማበረታቻ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ለሀገራችን የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላላቸውና ቅድሚያ ለሚሰጣቸው፣ እንዲሁም ከፍተኛ ካፒታል ለሚጠይቁ የኢንቨስትመንት መስኮች በሥራ ላይ የሚውለውን ካፒታል ከግምት ውስጥ የሚያስገባና በአፈጻጸም ላይ የተመሠረተ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል፣ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምፅ ወስኗል፡፡ 3. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ ፖሊሲው በኢንተርፕረነርሽፕ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት ቀጣይነት ኖሯቸው ለሀገራዊ የልማት ግቦች ስኬት ሚናቸውን እንዲወጡ፣ የፈጠራ ባህልን ለማጎልበትና እሴትን ለመጨመር የሚያስችል ምቹ የኢንተርፕረነርሽፕ ሥነ-ምህዳር ለመገንባት እንዲቻል ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል፣ ፖሊሲው በሚኒስትሮች ምክር ቤት ከጸደቀበት ከጥር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምፅ ወስኗል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ችግሮችን በመፍታት ሀገርን በጋራ የመገንባት ሂደትን ያሳልጣል
Jan 20, 2026 199
አምቦ፤ ጥር 12/2018 (ኢዜአ)፡- ችግሮችን በምክክር በመፍታት ሀገርን በጋራ የመገንባት ሂደት እውን እንዲሆን የጎላ ሚና ላለው ሀገራዊ ምክክር ስኬት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን አባገዳዎች ተናገሩ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መሠረታዊ የሆኑ ሀገራዊ የሐሳብ ልዩነቶችና አለመግባባቶችን ለመፍታት አካታች ምክክሮችን በማካሄድ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየሠራ ይገኛል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአምቦ ከተማ አባገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎችም፤ ምክክሩ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ወካይ ሐሳባቸውን የሚያቀርቡበት ትልቅ ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። አባገዳ ለገሠ ዳባ ምክክር የሚደገፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ በገዳ ሥርዓትም ምክክር ትልቅ ስፍራ እንደሚሰጠው አስገንዝበዋል። እየተካሄደ ባለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል እየተሳተፈ መሆኑን ተገንዝቤያለሁ ብለዋል። የከተማውን ሕብረተሰብ በመወከል በአዲስ አበባና አዳማ ከተሞች በምክክር ሂደቱ መሳተፋቸውን ገልጸው፤ በመድረኮቹ ለሀገር አንድነት የሚጠቅሙ ሐሳቦች መስጠታቸውን ገልጸዋል። በምክክሩ ዙሪያ ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ ሲፈጥሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው፤ ምክክሩ የታለመውን ውጤት እንዲያመጣ የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። አባ ገዳ ታሪኩ ቱራ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የቆዩ ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ የወደፊቷን ኢትዮጵያ የተሻለች ለማድረግ ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ዋናው ምክክርም በተሳካ መልኩ እንዲካሄድ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ገንቢ ሚና መጫወት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሚጠበቀውን ውጤት እንዲያመጣ ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ በማስጨበጥም ሆነ በሌሎች መንገዶች የድርሻቸውን እንደሚወጡ ጠቁመዋል። ምክክር መቀራረብን በማጠናከር የተሻለች ሀገር ለመገንባት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ያስገነዘቡት ደግሞ የሀገር ሽማግሌ በቀለ ባየታ ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን እንዲሁም የተጀመሩ ሀገራዊ ፕሮጀከቶች እንዲሳኩ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር በመሆኑ ለምክክሩ ስኬታማነት ድጋፋችን ይቀጥላል ብለዋል።
በክልሉ አደረጃጀቶችን በማጠናከር የልማትና የዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቷል
Jan 18, 2026 140
ባህርዳር ፤ ጥር 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል አደረጃጀቶችን በማጠናከር ልማትንና ዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አስታወቀ። "ጠንካራ አደረጃጀት ለጠንካራ ፓርቲ" በሚል መሪ ሃሳብ በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማውን እያካሄደ ነው። በፅህፈት ቤቱ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍስሃ ደሳለኝ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፤ አደረጃጀቶችን በማጠናከር ሁለንተናዊ ልማትንና ዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቷል። በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት የልማት አቅሞችን አቀናጅቶ በመስራት የታቀዱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በውጤታማነት ማከናወን መቻሉን አመልክተዋል። አደረጃጀቶች የፓርቲና የመንግስት ተልዕኮን መፈፀም ዋነኛ ግባቸው ነው ያሉት አቶ ፍስሃ፤ የክልሉን ሁለንተናዊ ልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማቀላጠፍ ግንባር ቀደም ሚናቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአደረጃጀቶች የጠራ ሃሳብና ግልጽ የትግበራ አቅጣጫ በመያዝ የልማት ስራዎችን ማከናወን የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መሰጠታቸውንም አስረድተዋል። በዚህም የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማሳካት አመራሩ ግንባር ቀደም ሆኖ መሰለፉን ተናግረዋል። ተግባሩም በቀጣይ የሀገሪቱን ብልጽግና ለማረጋገጥና ዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለመገንባት ተደማሪ አቅም መፍጠሩን አስረድተዋል። በመድረኩ ከክልል ጀምሮ በተዋረድ የሚገኙ የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች እየተሳተፉ እንደሚገኙም ታውቋል።
በአማራ ክልል በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን ዘረፋና እገታን የሃብት ምንጭ ያደረገ ነው
Jan 17, 2026 216
ባህር ዳር፤ ጥር 9/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን ዘረፋና እገታን የሃብት ምንጭ ያደረገ መሆኑን በቡድኑ አሻራ ሚዲያ ተብሎ የሚጠራው ሚዲያ ዋና ስራ አስኪያጅ የነበረው ኤሊያስ ደባሱ ተናገረ። ኤሊያስ በህዝብ ላይ ላደረሰው ጥፋት ይቅርታ በመጠየቅ የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የበደለውን ህዝብ ለመካስ መምጣቱን ገልጿል። በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን በህዝብ ላይ ግፍና በደል በመፈፀም በዘረፋ ሃብት ማካበት ላይ መሆኑን ተናግሯል። በዚህ የጥፋት ዓላማ በመሰለፍ በተለይም አመራር የሚሰጡ ግለሰቦች በገንዘብ ኪሳቸውን በማድለብ ሃብት እያካበቱ ይገኛሉ ብሏል። በተሳሳተ አረዳድ ለትግል በሚል ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በጫካ መቆየቱን አስታውሶ የጥፋት ቡድኑን አላማ በመረዳት ላደረሰው ጥፋትና በደል ይቅርታ በመጠየቅ መምጣቱን ገልጿል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ከክልሉ መንግስት ጋር ያደረገውን ስምምነት ተከትሎ በመምጣት የሰላም ስምምነቱ አካል መሆኑን ገልጿል። የሚዲያ ስራ ለመልካም ነገር ከዋለ ሀገር እንደሚገነባ የገለጸው ኤሊያስ ለጥፋት አላማ ጥቅም ላይ ከዋለ ደግሞ ጉዳቱ የከፋ መሆኑን አንስቶ በዚህ ረገድ ቡድኑ አሻራ ብሎ የሚጠራው ሚዲያ በክልሉ ህዝብ ላይ ጥፋት መፈፀሙን አስታውሷል። በሚዲያው “ያልደረስንበትን ከተማ ተቆጣጠርን፣ ያልተገደለን ሰው ተገደለ በማለት” የበዙ የፈጠራና የውሸት መረጃዎችን በማሰራጨት ሰዎችን አደናግረናል ያለው ኤሊያስ በዚህ ከባድ ጥፋት በመጸጸትም ይቅርታ ጠይቋል። በቀጣይ የሰላም አምባሳደርና የልማት አርበኛ በመሆን የበደልኩትን ህዝብ ለመካስ ተዘጋጅቻለሁ በማለት አሁንም በጫካ የሚገኙ ጊዜ ሳያባክኑ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።
ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍና ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ወሳኝ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል-አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Jan 17, 2026 177
አዲስ አበባ፤ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍና ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ወሳኝ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሚታዩ መሰረታዊ የሀሳብ ልዩነቶችን እና አለመግባባቶችን ለመፍታት አካታች በሆነ መልኩ ምክክር ለማካሄድ በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋቋመ ገለልተኛ ተቋም ነው፡፡ ኮሚሽኑ መሰረታዊ የሆኑ ሀገራዊ የሀሳብ ልዩነቶችንና አለመግባባቶችን አካታችና ሰፋፊ ህዝባዊ ምክክሮችን በማካሄድ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል፡፡ በዚህም ኮሚሽኑ ምክክር ማድረግ በሚቻልባቸው በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን በማከናወን ወደ መጨረሻው ምዕራፍ መድረሱ ይታወቃል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የኢትዮጵያ ጉዳይ ይገደናል ያሉ ኢትዮጵያውያን በንቃት የተሳተፉበት የምክክር ሂደት እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኮሚሽኑ በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በውጭ ሀገር ጭምር አጀንዳ በመሰብሰብና የዋናው ምክክር ሂደት ተሳታፊዎችን በመለየት ስኬታማ ስራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ በምክክር ሂደቱ ብዙሃን ማህበራት፣ሲቪል ማህበራት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ይበጃል ያሉትን ሀሳብ ያዋጡበት በዓይነቱ ልዩ እና ስኬታማ የምክክር ሂደት መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ የማጠቃለያ የምክክር ምዕራፉን ሂደት ተግባራዊ ለማድረግና ለመምራት የሚያስችል ስነ ዘዴ መቀረጹን ገልጸው፤ ቀሪ ስራ በተጀመረበት ስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ በኢትዮጵያ ከታሪክ፣ከህግ፣ ከአሰራር መሰል ጉዳዮች ጋር ተያይዞ የሚነሱ ነገሮች በምክክር ዕልባት ማግኘት የሚችሉ መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለዚህ ደግሞ ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ዕድል ነው ብለዋል፡፡ የትግራይ ክልልን በሚመለከት በሀገራዊ ምክክሩ ሊመለሱ የሚገባቸው ጥያቄዎች በተለያዩ አደረጃጀቶች መቅረባቸውን ገልጸዋል። በውይይቱ ብዙሃን ማህበራት፣ ሲቪል ማህበራትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ክልሉን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ማንሳታቸውን ገልጸው፤ የፖለቲካ ሀይሎችም ጥያቄያቸውን በሰነድ አቅርበዋል ብለዋል። ስለሆነም በትግራይ ክልል ያሉ ባለድርሻ አካላት እየተጠናቀቀ ባለው የምክክር ሂደት በንቃት በመሳተፍ ለምክክሩ ስኬት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ትልቅ አቅምና ሀብት ያላት ሀገር ነች ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ በንግግር፣በውይይትና በመተሳሰብ ተዓምር መሥራት እንችላለን ብለዋል፡፡ በዚህም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ ከማውጣትና ተቋም ከማቋቋም ጀምሮ ዕለታዊ ሥራዎችን እየተከታተለና እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከሀገራዊ ምክክሩ የሚገኘው ውጤት የህዝቡ ውሳኔ መሆኑን ያነሱት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ መንግሥት ውጤቱን ገቢራዊ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በምክክሩ ህዝብ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ተገቢውን አክብሮትና ምላሽ መስጠት ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የፍትሕ ዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ይቀጥላል
Jan 17, 2026 150
ጋምቤላ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡- የፍትሕ ዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል። በጋምቤላ ክልል የፍትሕ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አተገባበር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋምቤላ ከተማ ውይይት ተካሂዷል። በፍትሕ ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴዔታ የሆኑት ኡሞድ ኡጁሉ፤ የፍትሕ ዘርፉን ለማሻሻል የሶስት ዓመት የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተዘጋጅቶ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አሥተዳደሮች ተግባራዊ መደረጉን ገልጸዋል። በዚህም የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶች ለማስከበር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ስኬቶች እየተመዘገቡ ነው ብለዋል። የፍትሕ አገልግሎቱን ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ወጪ ቆጣቢ በማድረግ የሕዝቡን ርካታ ለማረጋገጥ የተሠሩ ሥራዎች ውጤታማ እንደነበሩም ጠቅሰዋል። በጋምቤላ ክልልም የፍትሕ ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ተግባራዊ በማድረግ የፍትሕ አገልግሎትን ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አበረታች መሆኑን አንስተዋል። በተለይም የፍትሕ አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር ውጤት የታየበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይም በይበልጥ መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ መሠረት ማቲዎስ በኩላቸው፤ የፍትሕ ተቋማት ዜጎች በፍትሕ ሥርዓቱ ያላቸውን ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ተግባራት ላይ አተኩረው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በተለይም ማኅበረሰብ አቀፍ የፍትሕ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ ያለው ተግባር ሊጠናክር ይገባል ብለዋል። በክልሉ ያለውን የፍትሕ ሥርዓት ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ኡዶል ኡኩሪ ናቸው። በክልሉ ፀድቆ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የፍትሕ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ፍኖተ ካርታ የዜጎች ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ ከማድረግ አንፃር አበርክቶው የጎላ መሆኑንም አብራርተዋል።
ፖለቲካ
ምክር ቤቱ የምርጫ አዋጁን በማሻሻል በቴክኖሎጂ የታገዘ ግልጽና ፍትሐዊ ምርጫ እንዲካሄድ አስቻይ ሁኔታዎችን ፈጥሯል
Jan 21, 2026 88
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ አዋጁን በማሻሻል፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ግልጽ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ምርጫ ማከናወን የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ማድረጉን የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲከናወንና ድምፅ መስጫውም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሆን መወሰኑ ይታወሳል። ቦርዱ ይህንን ታሳቢ በማድረግ ከግብዓት ማሟላት እስከ ሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች የተለያዩ ዝግጅቶችን ማድረጉን አስታውቋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሀገሪቱ ምርጫና ድምጸ-ውሳኔ የሚያካሂድ ገለልተኛ ሕገ-መንግሥታዊ ተቋም ነው። ቦርዱ በሕገ-መንግሥቱ መሠረት 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ በቂ ዝግጅት ማድረጉን በሪፖርቱ ማረጋገጡን ገልጸዋል። ምክር ቤቱ 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊና ተዓማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊ የሕግ ማሻሻያዎች ማድረጉን ጠቁመዋል። በተለይም አዋጅ ቁጥር 1162/2011ን በማሻሻል የዕጩዎችና የመራጮች ምዝገባ እንዲሁም ሌሎች የቦርዱ ሥራዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ እንዲሆኑ አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን አብራርተዋል። የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ምርጫውን በመታዘብና ለመራጮች ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ወሳኝ ሚና እንዳላቸውም ገልጸዋል። መንግሥት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሠረት የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት የሚያሳልጡ ዝግጅቶችን እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በብሔራዊ መግባባት እንዲከናወን ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቀሰው ለምርጫው ስኬታማነት ሁሉም አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን በማረጋገጥ ረገድ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እያስመዘገበች ነው
Jan 20, 2026 148
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የወል ትርክትን በመገንባትና ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ ረገድ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እያስመዘገበች መሆኗን የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ያሏት ፀጋዎች ሁለንተናዊ ዕድገትን ለማምጣት እና ዜጎችን የሚያስተሳስር የጋራ ትርክት ለመገንባት ወሳኝ ናቸው። እነዚህን ፀጋዎች በውል ተገንዝቦ ሀገራዊ ፋይዳ ላለው ተግባር ማዋል ባለመቻሉ እና በሚያስተሳስሩን ጉዳዮች ላይ ትኩረት ባለመደረጉ ሀገራዊ ዕድገት ተገድቦ ቆይቷል ብለዋል። በአንፃሩ አሁን ላይ ተገቢውን ትኩረት ያገኘው የጋራ ትርክት ጉዳይ እነዚህን ማነቆዎች በመፍታት ለሀገር ብልጽግና መሠረት እንደሚሆን አመላክተዋል። የለውጡ መንግሥት አብሮነትን የሚያጎሉ የጋራ ትርክት ግንባታ ላይ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተጽፈው ለንባብ የበቁት የመደመር መጻሕፍት፤ ዜጎች ስለ ሀገራቸው ያላቸውን አረዳድ በማስተካከልና የወል ትርክትን በመቅረጽ ረገድ ትልቅ ሚና አላቸው ብለዋል። በሀገሪቱ በተግባር ዕየታዩ የሚገኙ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶች የዜጎችን አንድነት ከማጠናከር ባለፈ ውስጣዊ ጥንካሬንና ብሔራዊ ኩራትን ማጎልበት የሚችል ዐቅም መፈጠሩንም ተናግረዋል፡፡ ይህም ለትውልድ ቀረጻና ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚውል የጋራ ትርክት የመፍጠር ሥራ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ያመላክታል ነው ያሉት። ፈጠራ የታከለበት የመንግሥት ፈጣን አስተሳሳሪ የልማት አካሄድ፤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን በዓለም አቀፍ ደረጃ እንድታስከብር ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው በአጽንኦት አንስተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከናወኑ የብሔራዊ ትርክት ግንባታ ሥራዎች ኢትዮጵያ ውስጣዊ አንድነቷን እንድታጠናክርና ጥቅሞቿን እንድታስከብር ዕድል መፍጠራቸውንም ጠቁመዋል። ይህም ሀገሪቱ ሉዓላዊነቷንና ጥቅሟን በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሀገራዊ የከፍታ ምዕራፍ ላይ መድረሷን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብና የባሕር በር ባለቤትነትን የማረጋገጥ ጥረቶችን በዋነኛ ማሳያነት ጠቅሰዋል። እነዚህም ኢትዮጵያ ያላትን ትልቅ ዐቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያስመሰከሩና ዜጎችን በአንድ የጋራ ዓላማ ሥር ያሰለፉ መሆናቸው ነው የገለጹት። በሕዳሴ ግድብ አማካኝነት ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት በቀጣናዊ የኃይል ትስስር ረገድ ያበረከተችውን ሚና ዓለም እንዲያውቀው አስችሏልም ብለዋል። ፍትሐዊ የባሕር በር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ታሪካዊ ግስጋሴም፣ የጋራ ትርክት መገንባት ዜጎችን በአንድ ልብ ለማሰለፍ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
Jan 20, 2026 135
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 52ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ምክር ቤቱ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች እንደሚከተለው ቀርቧል፦ 52ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች ጥር 12 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 52ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ በሥራ ላይ ያለው የጉምሩክ አዋጅ ለበርካታ ዓመታት ያገለገለ በመሆኑ፣ የአዋጁን ድንጋጌዎች ዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ከደረሰበት የዕድገት ደረጃ ጋር ለማጣጣም፣ በአገራችን እያደገ የመጣውን የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ለመደገፍ፣ እንዲሁም ሕጋዊ ንግድንና ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት ይቻል ዘንድ የማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል አዋጁ ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምፅ ወስኗል፡፡ 2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው ለኢንቨስትመንት ስለሚሰጥ የታክስና ቀረጥ ማበረታቻ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ለሀገራችን የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላላቸውና ቅድሚያ ለሚሰጣቸው፣ እንዲሁም ከፍተኛ ካፒታል ለሚጠይቁ የኢንቨስትመንት መስኮች በሥራ ላይ የሚውለውን ካፒታል ከግምት ውስጥ የሚያስገባና በአፈጻጸም ላይ የተመሠረተ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል፣ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምፅ ወስኗል፡፡ 3. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ ፖሊሲው በኢንተርፕረነርሽፕ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት ቀጣይነት ኖሯቸው ለሀገራዊ የልማት ግቦች ስኬት ሚናቸውን እንዲወጡ፣ የፈጠራ ባህልን ለማጎልበትና እሴትን ለመጨመር የሚያስችል ምቹ የኢንተርፕረነርሽፕ ሥነ-ምህዳር ለመገንባት እንዲቻል ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል፣ ፖሊሲው በሚኒስትሮች ምክር ቤት ከጸደቀበት ከጥር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምፅ ወስኗል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ችግሮችን በመፍታት ሀገርን በጋራ የመገንባት ሂደትን ያሳልጣል
Jan 20, 2026 199
አምቦ፤ ጥር 12/2018 (ኢዜአ)፡- ችግሮችን በምክክር በመፍታት ሀገርን በጋራ የመገንባት ሂደት እውን እንዲሆን የጎላ ሚና ላለው ሀገራዊ ምክክር ስኬት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን አባገዳዎች ተናገሩ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መሠረታዊ የሆኑ ሀገራዊ የሐሳብ ልዩነቶችና አለመግባባቶችን ለመፍታት አካታች ምክክሮችን በማካሄድ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየሠራ ይገኛል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአምቦ ከተማ አባገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎችም፤ ምክክሩ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ወካይ ሐሳባቸውን የሚያቀርቡበት ትልቅ ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። አባገዳ ለገሠ ዳባ ምክክር የሚደገፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ በገዳ ሥርዓትም ምክክር ትልቅ ስፍራ እንደሚሰጠው አስገንዝበዋል። እየተካሄደ ባለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል እየተሳተፈ መሆኑን ተገንዝቤያለሁ ብለዋል። የከተማውን ሕብረተሰብ በመወከል በአዲስ አበባና አዳማ ከተሞች በምክክር ሂደቱ መሳተፋቸውን ገልጸው፤ በመድረኮቹ ለሀገር አንድነት የሚጠቅሙ ሐሳቦች መስጠታቸውን ገልጸዋል። በምክክሩ ዙሪያ ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ ሲፈጥሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው፤ ምክክሩ የታለመውን ውጤት እንዲያመጣ የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። አባ ገዳ ታሪኩ ቱራ በበኩላቸው፤ የሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የቆዩ ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ የወደፊቷን ኢትዮጵያ የተሻለች ለማድረግ ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ዋናው ምክክርም በተሳካ መልኩ እንዲካሄድ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ገንቢ ሚና መጫወት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሚጠበቀውን ውጤት እንዲያመጣ ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ በማስጨበጥም ሆነ በሌሎች መንገዶች የድርሻቸውን እንደሚወጡ ጠቁመዋል። ምክክር መቀራረብን በማጠናከር የተሻለች ሀገር ለመገንባት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ያስገነዘቡት ደግሞ የሀገር ሽማግሌ በቀለ ባየታ ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን እንዲሁም የተጀመሩ ሀገራዊ ፕሮጀከቶች እንዲሳኩ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር በመሆኑ ለምክክሩ ስኬታማነት ድጋፋችን ይቀጥላል ብለዋል።
በክልሉ አደረጃጀቶችን በማጠናከር የልማትና የዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቷል
Jan 18, 2026 140
ባህርዳር ፤ ጥር 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል አደረጃጀቶችን በማጠናከር ልማትንና ዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አስታወቀ። "ጠንካራ አደረጃጀት ለጠንካራ ፓርቲ" በሚል መሪ ሃሳብ በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማውን እያካሄደ ነው። በፅህፈት ቤቱ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍስሃ ደሳለኝ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፤ አደረጃጀቶችን በማጠናከር ሁለንተናዊ ልማትንና ዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቷል። በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት የልማት አቅሞችን አቀናጅቶ በመስራት የታቀዱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በውጤታማነት ማከናወን መቻሉን አመልክተዋል። አደረጃጀቶች የፓርቲና የመንግስት ተልዕኮን መፈፀም ዋነኛ ግባቸው ነው ያሉት አቶ ፍስሃ፤ የክልሉን ሁለንተናዊ ልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማቀላጠፍ ግንባር ቀደም ሚናቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአደረጃጀቶች የጠራ ሃሳብና ግልጽ የትግበራ አቅጣጫ በመያዝ የልማት ስራዎችን ማከናወን የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መሰጠታቸውንም አስረድተዋል። በዚህም የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማሳካት አመራሩ ግንባር ቀደም ሆኖ መሰለፉን ተናግረዋል። ተግባሩም በቀጣይ የሀገሪቱን ብልጽግና ለማረጋገጥና ዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለመገንባት ተደማሪ አቅም መፍጠሩን አስረድተዋል። በመድረኩ ከክልል ጀምሮ በተዋረድ የሚገኙ የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች እየተሳተፉ እንደሚገኙም ታውቋል።
በአማራ ክልል በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን ዘረፋና እገታን የሃብት ምንጭ ያደረገ ነው
Jan 17, 2026 216
ባህር ዳር፤ ጥር 9/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን ዘረፋና እገታን የሃብት ምንጭ ያደረገ መሆኑን በቡድኑ አሻራ ሚዲያ ተብሎ የሚጠራው ሚዲያ ዋና ስራ አስኪያጅ የነበረው ኤሊያስ ደባሱ ተናገረ። ኤሊያስ በህዝብ ላይ ላደረሰው ጥፋት ይቅርታ በመጠየቅ የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የበደለውን ህዝብ ለመካስ መምጣቱን ገልጿል። በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን በህዝብ ላይ ግፍና በደል በመፈፀም በዘረፋ ሃብት ማካበት ላይ መሆኑን ተናግሯል። በዚህ የጥፋት ዓላማ በመሰለፍ በተለይም አመራር የሚሰጡ ግለሰቦች በገንዘብ ኪሳቸውን በማድለብ ሃብት እያካበቱ ይገኛሉ ብሏል። በተሳሳተ አረዳድ ለትግል በሚል ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በጫካ መቆየቱን አስታውሶ የጥፋት ቡድኑን አላማ በመረዳት ላደረሰው ጥፋትና በደል ይቅርታ በመጠየቅ መምጣቱን ገልጿል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ከክልሉ መንግስት ጋር ያደረገውን ስምምነት ተከትሎ በመምጣት የሰላም ስምምነቱ አካል መሆኑን ገልጿል። የሚዲያ ስራ ለመልካም ነገር ከዋለ ሀገር እንደሚገነባ የገለጸው ኤሊያስ ለጥፋት አላማ ጥቅም ላይ ከዋለ ደግሞ ጉዳቱ የከፋ መሆኑን አንስቶ በዚህ ረገድ ቡድኑ አሻራ ብሎ የሚጠራው ሚዲያ በክልሉ ህዝብ ላይ ጥፋት መፈፀሙን አስታውሷል። በሚዲያው “ያልደረስንበትን ከተማ ተቆጣጠርን፣ ያልተገደለን ሰው ተገደለ በማለት” የበዙ የፈጠራና የውሸት መረጃዎችን በማሰራጨት ሰዎችን አደናግረናል ያለው ኤሊያስ በዚህ ከባድ ጥፋት በመጸጸትም ይቅርታ ጠይቋል። በቀጣይ የሰላም አምባሳደርና የልማት አርበኛ በመሆን የበደልኩትን ህዝብ ለመካስ ተዘጋጅቻለሁ በማለት አሁንም በጫካ የሚገኙ ጊዜ ሳያባክኑ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።
ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍና ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ወሳኝ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል-አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Jan 17, 2026 177
አዲስ አበባ፤ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍና ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ወሳኝ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሚታዩ መሰረታዊ የሀሳብ ልዩነቶችን እና አለመግባባቶችን ለመፍታት አካታች በሆነ መልኩ ምክክር ለማካሄድ በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋቋመ ገለልተኛ ተቋም ነው፡፡ ኮሚሽኑ መሰረታዊ የሆኑ ሀገራዊ የሀሳብ ልዩነቶችንና አለመግባባቶችን አካታችና ሰፋፊ ህዝባዊ ምክክሮችን በማካሄድ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል፡፡ በዚህም ኮሚሽኑ ምክክር ማድረግ በሚቻልባቸው በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን በማከናወን ወደ መጨረሻው ምዕራፍ መድረሱ ይታወቃል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የኢትዮጵያ ጉዳይ ይገደናል ያሉ ኢትዮጵያውያን በንቃት የተሳተፉበት የምክክር ሂደት እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኮሚሽኑ በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በውጭ ሀገር ጭምር አጀንዳ በመሰብሰብና የዋናው ምክክር ሂደት ተሳታፊዎችን በመለየት ስኬታማ ስራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ በምክክር ሂደቱ ብዙሃን ማህበራት፣ሲቪል ማህበራት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ይበጃል ያሉትን ሀሳብ ያዋጡበት በዓይነቱ ልዩ እና ስኬታማ የምክክር ሂደት መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ የማጠቃለያ የምክክር ምዕራፉን ሂደት ተግባራዊ ለማድረግና ለመምራት የሚያስችል ስነ ዘዴ መቀረጹን ገልጸው፤ ቀሪ ስራ በተጀመረበት ስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ በኢትዮጵያ ከታሪክ፣ከህግ፣ ከአሰራር መሰል ጉዳዮች ጋር ተያይዞ የሚነሱ ነገሮች በምክክር ዕልባት ማግኘት የሚችሉ መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለዚህ ደግሞ ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ዕድል ነው ብለዋል፡፡ የትግራይ ክልልን በሚመለከት በሀገራዊ ምክክሩ ሊመለሱ የሚገባቸው ጥያቄዎች በተለያዩ አደረጃጀቶች መቅረባቸውን ገልጸዋል። በውይይቱ ብዙሃን ማህበራት፣ ሲቪል ማህበራትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ክልሉን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ማንሳታቸውን ገልጸው፤ የፖለቲካ ሀይሎችም ጥያቄያቸውን በሰነድ አቅርበዋል ብለዋል። ስለሆነም በትግራይ ክልል ያሉ ባለድርሻ አካላት እየተጠናቀቀ ባለው የምክክር ሂደት በንቃት በመሳተፍ ለምክክሩ ስኬት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ትልቅ አቅምና ሀብት ያላት ሀገር ነች ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ በንግግር፣በውይይትና በመተሳሰብ ተዓምር መሥራት እንችላለን ብለዋል፡፡ በዚህም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ ከማውጣትና ተቋም ከማቋቋም ጀምሮ ዕለታዊ ሥራዎችን እየተከታተለና እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከሀገራዊ ምክክሩ የሚገኘው ውጤት የህዝቡ ውሳኔ መሆኑን ያነሱት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ መንግሥት ውጤቱን ገቢራዊ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በምክክሩ ህዝብ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ተገቢውን አክብሮትና ምላሽ መስጠት ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የፍትሕ ዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ይቀጥላል
Jan 17, 2026 150
ጋምቤላ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡- የፍትሕ ዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል። በጋምቤላ ክልል የፍትሕ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አተገባበር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋምቤላ ከተማ ውይይት ተካሂዷል። በፍትሕ ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴዔታ የሆኑት ኡሞድ ኡጁሉ፤ የፍትሕ ዘርፉን ለማሻሻል የሶስት ዓመት የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተዘጋጅቶ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አሥተዳደሮች ተግባራዊ መደረጉን ገልጸዋል። በዚህም የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶች ለማስከበር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ስኬቶች እየተመዘገቡ ነው ብለዋል። የፍትሕ አገልግሎቱን ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ወጪ ቆጣቢ በማድረግ የሕዝቡን ርካታ ለማረጋገጥ የተሠሩ ሥራዎች ውጤታማ እንደነበሩም ጠቅሰዋል። በጋምቤላ ክልልም የፍትሕ ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ተግባራዊ በማድረግ የፍትሕ አገልግሎትን ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አበረታች መሆኑን አንስተዋል። በተለይም የፍትሕ አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር ውጤት የታየበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይም በይበልጥ መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ መሠረት ማቲዎስ በኩላቸው፤ የፍትሕ ተቋማት ዜጎች በፍትሕ ሥርዓቱ ያላቸውን ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ተግባራት ላይ አተኩረው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በተለይም ማኅበረሰብ አቀፍ የፍትሕ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ ያለው ተግባር ሊጠናክር ይገባል ብለዋል። በክልሉ ያለውን የፍትሕ ሥርዓት ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ኡዶል ኡኩሪ ናቸው። በክልሉ ፀድቆ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የፍትሕ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ፍኖተ ካርታ የዜጎች ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ ከማድረግ አንፃር አበርክቶው የጎላ መሆኑንም አብራርተዋል።
ማህበራዊ
የጤና ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉና ደረጃቸውን ያልጠበቁ የጨው ምርቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ
Jan 21, 2026 73
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ በህብረተሰቡ ላይ የጤና ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉና ደረጃቸውን ያልጠበቁ የጨው ምርቶች ላይ እርምጃ መውሰዱን የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ። ባለሥልጣኑ ባከናወነው የተቀናጀ ክትትል በመጋዘን የተከማቹ ህገወጥ የጨው ምርቶችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ነጋሽ ስሜ እንደተናገሩት ባለሥልጣኑ ደህንነቱና ጥራቱ የተረጋገጠ ምርት ለህብረተሰቡ ተደራሽ እንዲሆን በትኩረት እየሰራ ነው። በዚህም ሙሉ በሙሉና በከፊል የተቀነባበሩ ምርቶች ላይ የሚደረገው ቁጥጥር ተጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል። ባለሥልጣኑ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር ባደረገው ጥብቅና የተቀናጀ ቁጥጥር በሸገር ከተማ ፉሪ ክፍለ ከተማ በሚገኙ አፋር፣ አፊዴር ወለላ እና በሩዋቅ በተሰኙ ሦስት የጨው ምርቶች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። በዚህም ከ13 ሺህ ኩንታል በላይ ደረጃውን ያልጠበቀ የጨው ምርት በቁጥጥር ሥር መዋሉን ገልፀዋል። ምርቶቹ የተቀመጠውን ብሔራዊ የአዮዲን ይዘት መስፈርት ሳያሟሉ የተመረቱ እንዲሁም ጨው ለምግብነት ከመቅረቡ በፊት መከናወን ያለበት የማጠብና የማጽዳት ሂደት ሳይደረግላቸው ለገበያ የቀረቡ መሆናቸውን አንስተዋል። ምርቶቹ ለሰው ልጅ ጤና ጎጂ የሆኑ ባዕድ ነገሮችን ሊይዙ የሚችሉ መሆናቸውንም ነው ጨምረው የተናገሩት። ባለሥልጣኑ ከጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት መሰል የክትትል ስራዎችን በሌሎች የምርት ዘርፎች ላይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡ ሕብረተሰቡም ጥራታቸው የተረጋገጡ ምርቶችን ብቻ በመጠቀም ለጤናው ጥንቃቄ እንዲያደርግ አስገንዝበዋል።
ሀገራዊ ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የጋራ መፍትሄ ለማምጣት የሀገራዊ ምክክሩ ፋይዳ ከፍተኛ ነው -- አባገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌ እና ሀደ ሲንቄ
Jan 21, 2026 80
ሮቤ ፤ ጥር 13/2018(ኤዜአ)፡- ሀገራዊ ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የጋራ መፍትሄ ለማምጣት የሀገራዊ ምክክሩ ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን የባሌ ዞን አባገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌ እና ሃደ ሲንቄ ተናገሩ። በኢትዮጵያ እየተንከባለሉ የመጡ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አካታችና ሰፋፊ ህዝባዊ ምክክሮችን በማካሄድ መግባባትን ለመፍጠር እየሰራ ነው፡፡ በሂደቱም እስካሁን ኮሚሽኑ ምክክር ማድረግ በሚቻልባቸው ሀገራዊ ጉዳዮች የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎችን በማገባደድ ላይ ይገኛል። ጉዳዩን በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው የባሌ ዞን አባገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ሃደ ሲንቄዎች ሀገራዊ ምክክሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ሲያሳትፍ መቆየቱን መታዘባቸውን ተናግረዋል። የጋሠራ ወረዳ አባገዳ መሐመድ አሎ እንዳሉት የምክክር መድረኩ በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበርና ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በመገንዘብ በሂደቱ በንቃት ሲሳተፉ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በእስከ አሁኑ ሂደትም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መልኩ ለሀገር ይጠቅማሉ የተባሉ ሀሳቦች መሰብሰቡ እጅግ የሚበረታታ መሆኑን ጠቅሰው ሀገራዊ ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የጋራ መፍትሄ ለማምጣት የሀገራዊ ምክክሩ ፋይዳ ከፍተኛ ነው ብለዋል። የአጋርፋ ወረዳ ሃደ ሲንቄ መኮ ሐጅ አደም ተመሳሳይ ሀሳብ በመጋራት የሀገራዊ ምክክሩ መሳካት በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን በምክክር በመፍታት የጋራ መፍትሄ ለማበጀት ይረዳል ሲሉ ገልጸዋል። የወረዳቸውን ህብረተሰብ በመወከል በአዳማ ከተማ በምክክር ሂደቱ የተሳተፉ ሲሆን በመድረኮቹ ለአገር አንድነት የሚጠቅሙ ሀሳቦችን መስጠታቸውን አስረድተዋል። በአጀንዳ ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ በመሳተፍ ለሀገር ይበጃል ያሉትን የመፍትሔ ሃሳብ በነፃነት ማቅረባቸውና ሂደቱም ግልጽና አሳታፊ እንደነበረ የገለጹት ደግሞ የጎሮ ወረዳ የሀገር ሽማግሌው ሼህ ቡሽራ ሼህ ኡስማን ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩ መግባባት እና መቀራረብን በማጠናከር ወደ ፊት የተሻለች ሀገር ለመገንባት ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ ለምክክሩ ስኬታማነት ድጋፋችን ይቀጥላል ብለዋል።
ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት በጽናት መቆም ይገባል
Jan 20, 2026 97
ወላይታ ሶዶ ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ):- የጀግኖችን ፈለግ በመከተልና ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት በጽናት መቆም አለብን ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ። ወላይታን ከ1858 እስከ 1887 ዓ.ም ላስተዳደሩትና የወላይታ የመጨረሻው ንጉስ ለነበሩት ካዎ ጦና የተገነባ የመታሰቢያ ሃውልት ተመርቋል። በምረቃው ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ ገብረመስቀል ጫላ እንደገለጹት የጀግኖችን ፈለግ በመከተልና ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት በጽናት መቆም አለብን። ካዎ ጦና በንግስና ጊዜያቸው የህዝቦች አንድነትና ሀገር ወዳድነት እንዲጠናከር መስራታቸውን አስታውሰው ታሪኮችን በመጠበቅ አሰባሳቢና የወል ትርክቶችን በመገንባት ለትውልድ የሚሻገር ታሪክ ማስቀመጥ ተችሏል ብለዋል። የአሁኑ ትውልድም በተሰማራባቸው መስኮች ሁሉ ሀገሩንና ህዝብን በታማኝነት ማገልገልን ከእርሳቸው ትምህርት መውሰድ አለበት ሲሉም ተናግረዋል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ እታገኝ ኃይለማሪያም በበኩላቸው፣ የካዎ ጦና የጀግንነትና የልማት ታሪክ ለሀገር ዕድገትና ፍቅር እንዲኖረን የሚያስተምር መሆኑን ገልጸዋል። ንጉስ ጦና ከ131 ዓመታት በኋላ ወላይታን አንድ አድርገው ለመሩበት እና በዓድዋ ድል ጊዜ ዘምተው ላበረከቱት ሀገራዊ አስተዋጽኦ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ሐውልት መሠራቱን ተናግረዋል። የሀውልቱ መቆም በህዝብ ዘንድ አንድነትን በመፍጠር በዞኑና በወላይታ ሶዶ ከተማ የተጀመሩ ልማቶችን ከግብ ለማድረስ መነሳሳትን ይፈጥራል ብለዋል። የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በበኩላቸው ጀግኖችን መዘከርና ታሪክን ማወቅ ያለፈውን በመተንተን ከስህተቶች ለመማርና መልካሙን ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል። የህዝቦችን ባህልና ታሪክ ቀጣይነት ለማረጋገጥ ቀደምት ባለውለታዎችን መዘከር እንደሚያስፈልግ ገልጸው፣ በጥንታዊው የወላይታ መንግስት ግንባታ ሂደት ህዝቡ በአንድነት ቆሞ የማይረሳ ታሪክ መስራቱን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም ህዝቡ ከመሪዎቹ ጋር በአንድነት በመቆም የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት መትጋት ይኖርበታል ብለዋል።
ሀገራዊ ምክክር ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መፍትሄ በመሆኑ ለስኬቱ ድጋፋችንን እናጠናክራለን
Jan 20, 2026 126
ጂንካ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክር ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መፍትሄ በመሆኑ ለስኬታማነቱ ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ በጂንካ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ገለጹ። በኢትዮጵያ ካሉ ባህላዊ እሴቶች መካከል ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርአት አንዱ ሲሆን ይህም ለዘመናዊ የፍትህ ስርአት ጉልህ እስተዋጽኦ ያበረክታል። በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር እየተካሄደ ባለው ሀገራዊ ምክክር ሂደት ሀገር በቀል የግጭት መፍቻ ዘዴዎችን መጠቀም ያማረ ውጤት እንደሚያስገኝም ነው የሚገለጸው። በጉዳዩ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጂንካ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች እነዚህን ባህላዊ እሴቶች በአግባቡ በመጠቀም ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የሚያደርጉትን ድጋፍና እገዛ እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል። ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍና ስኬታማ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቶ ወሳኝ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ የደረሰው ሀገራዊ ምክክሩለሀገር ዘላቂ ሰላም አምጥቶ የማየት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የጂንካ ከተማ የሀገር ሽማግሌ ዳኜ ገብሬ እንዳሉት ሀገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መፍትሄ ነው። የቆዩና የማያግባቡ ችግሮች ላይ በጋራ በመምከር ሀገራዊ መግባባት እንዲመጣ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ወደ ሥራ መገባቱና ሂደቱ ሁሉንም ያሳተፈ መሆኑ የዴሞክራሲ ስርአት ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ሀገር በቀል ችግሮች የሚፈቱት በሀገር በቀል እሴቶች መሆኑን ጠቁመው፣ በኮሚሽኑ የእስካሁኑ ሂደት በአካባቢያቸው ህብረተሰቡን በማስገንዘብና የኮሚሽኑ መድረኮች ላይ በንቃት በመሳተፍ ለምክክሩ ሂደት አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በጂንካ ከተማ የሚገኘው የኔሪ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማሪያም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መላከ አርያም ቀሲስ ዱባለ ፍሬው በበኩላቸው ሀገር የምትፀናው በምክክር በመሆኑ በማያግባቡ ችግሮች ላይ መወያየትና መፍትሔ ማበጀት መልካም ሀሳብ ነው ብለዋል። የምክክር ሂደቱ እስከመጨረሻው ስኬታማ እንዲሆን ምዕመኑን ስለሰላምና አብሮነት ከማስተማር በተጨማሪ በምክክሩ ተሳትፎውን እንዲያጠናክር በማስተባበር ጭምር ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። በሀገር ግንባታ የሁሉም ዜጋ ሀሳብና ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በጂንካ ከተማ የሚገኘው የመስጂድ-ሰላም ኢማም ሼህ ኢድሪስ አህመድ ናቸው። ለትውልዱ የሚበጅ፣ ሀገርን የሚጠቅምና የሚያሳድግ ሀሳብ ያለው ዜጋ ሀሳቡን በማዋጣት ለሀገር ግንባታው የራሱን አሻራ ማኖር ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ ሀገር ሰላሟ ጸንቶ ልማቷ እንዲፋጠን እንደ ሃይማኖት አባት ምዕመናን ሰላምና አንድነታቸውን እንዲያጸኑ የማስተማር ሚናቸውን እንደሚወጡ ገልጸው፣ ወደ መገባደድ ደረጃ የደረሰው የምክክር ሂደቱ ስኬታማ ሆኖ የምንፈልገውን ሰላምና ዕድገት እንዲያመጣ ሁላችንም እገዛችንን ማጠናከር አለብን ሲሉ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ውጤታማ የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን በማከናወን ወደ መጨረሻው የምክክር ምዕራፍ በመድረሱ ለመጨረሻው ስኬት ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንዳለበትም አመልክተዋል።
ኢኮኖሚ
በጎንደር ከተማ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ለ142 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ ተሰጥቷል
Jan 21, 2026 40
ጎንደር ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ በጎንደር ከተማ በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከ43 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 142 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ገለጸ። በጎንደር ከተማ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ባለሀብቶች፣ ዳያስፖራዎችና ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የኢንቨስትመንት ፎረም ተካሂዷል። በዚሁ ጊዜ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ ግርማይ ልጃለም፤ ፎረሙ ከተማዋ ያላትን የልማት ጸጋዎች ለማስተዋወቅና አዳዲስ ባለሃብቶችን ለመሳብ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በከተማዋ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 142 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል። ፈቃድ የተሰጣቸው ባለሃብቶች በአምራች ኢንዱስትር፣ በግብርናና በአገልግሎት ዘርፍ የሚሰማሩ መሆኑንም ተናግረዋል። እነዚህ ባለሃብቶች ወደ ሥራ ሲገቡ በከተማዋ ለሚገኙ 29 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ በመግለጽ። እስካሁን ባለው ሂደት ለ17 ባለሃብቶች 17 ሄክታር የግንባታ ቦታ መሰጠቱን ጠቅሰው፣ ወደ ግንባታ ለገቡ 22 አምራች ኢንዱስትሪዎች የመብራት፣ የውሃና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መሟላቱን አመልክተዋል። በከተማዋ የተከናወኑ የቱሪዝምና የኮሪደር ልማት ሥራዎች በርካታ ባለሀብቶች መዕዋለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ነው የመምሪያው ኃላፊ የተናገሩት። በመምሪያው የኢንዱስትሪ ልማት ቡድን መሪ ፋሲል ዘውዱ ባቀረቡት የውይይት መነሻ፤ በከተማዋ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሃብቶች ምቹ ምህዳር ተፈጥሯል ብለዋል። በኢንዱስትሪ መንደር ውስጥ ከ700 ሄክታር በላይ ቦታ መዘጋጀቱን ለአብነት አንስተዋል። የግንባታ ፍቃድ ወስደው ግንባታ ያልጀመሩና ቦታውን አጥረው በቆዩ ባለሃብቶች ላይ አስፈላጊው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አመልክተው፣7 ባለሃብቶች የወሰዱትን መሬት ባለማልማታቸው ወደ መሬት ባንክ ገቢ መደረጉን ተናግረዋል። የፎረሙ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፣ በከተማዋ እየታየ ያለው ሰላምና መረጋጋት ለኢንቨሰትመንት አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ሲሳይ ወንድሙና ዘይኑ መሀመድ ከተማዋ ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆኗን አንስተዋል። ከኢንቨስትመንት ፍቃድ አሰጣጥ ጀምሮ ያለው ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት የባለሀብቶችን ቀልብ የሚስብ ነው ብለዋል።
በወራቤ ከተማ ግንባታው እየተከናወነ ያለው የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ የከተማዋን እድገት እያፋጠነ ነው
Jan 21, 2026 30
ወራቤ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ በወራቤ ከተማ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ግንባታው እየተከናወነ ያለው የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ የከተማዋን እድገት እያፋጠነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሻፊ ሙዜ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማዋ በራስ አቅምና በህብረተሰቡ ተሳትፎ በ1 ቢሊዮን 610 ሚሊዮን ብር 5 ነጥብ 73 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ እየተገነባ ነው። ከከተማ የውስጥ ለውስጥ አስፓልት መንገድ ሥራ ጎን ለጎንም የፍሳሽ ማስወገጃ ትቦ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው። በሁለት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ታቅዶ ወደ ተግባር ከተገባው የመንገድ ስራም ውስጥ 1 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትሩ ለአስፓልት ንጣፍ ዝግጁ መደረጉን ገልጸዋል። የአስፓልቱ ግንባታ ሥራ በከተማው በ1 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እየለማ የሚገኘውን የሶጃት ኢንዱስትሪ መንደርን ጨምሮ ሌሎች አካባቢዎችን እንደሚያገናኝም ተናግረዋል። የአስፓልት መንገድ ግንባታ ሥራውን በታቀደለት ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ በከተማው የቀበሌ 01 ነዋሪ አቶ ጅብሪል አማን ለኢዜአ እንዳሉት፤ በከተማ አስተዳደሩና በህብረተሰቡ ተሳትፎ እየተሰራ ያለው የውስጥ ለውስጥ አስፓልት መንገድ ግንባታ ለከተማው የንግድ ሥራ መነቃቃት ከመፍጠር ባለፈ የትራንስፖርት ፍሰቱን እንደሚያቀላጥፈው ተናግረዋል፡፡ ለአስፓልት መንገዱ ሥራ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ገልፀዋል፡፡ ሌላው የዚሁ ከተማ ነዋሪ አቶ ሸረፈዲን ሹሜ እንደገለጹት፤ ለአንድ አካባቢ ፈጣን እድገት መረጋገጥ የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ማስፋት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው። የከተማው አስተዳደር እያከናወነ ያለው ተግባር በከተማዋ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና የከተማዋን ፈጣን እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝም ተናግረዋል፡፡
የንግድ ስርዓቱን ለማዘመንና የግብይት ማዕከላትን ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቷል
Jan 21, 2026 61
ኮምቦልቻ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ ገበያውን ለማረጋጋት የንግድ ስርዓቱን ለማዘመንና የግብይት ማዕከላትን ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ። በኮምቦልቻ ከተማ በ120 ሚሊየን ብር የተገነባው የገበያ ማዕከል ተመርቋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በተበታተነ መንገድ የሚደረግ ግብይትን በማሰባሰብና የግብይት ስርዓቱን በማዘመን የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት እየተሰራ ነው። በተጨማሪም የግብይት ስፍራዎችን ማልማት፣ ይዞታቸውን ማስከበር እንዲሁም ደረጃቸውን በማሻሻል ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በከተሞች የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ተቋቁመው ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እና በቅናሽ እንዲቀርብ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ዛሬ በኮምቦልቻ ከተማ የተመረቀው የገበያ ማዕከልም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰው ስራው በሌሎች ከተሞችም መስፋት እንዳለበት ጠቁመዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የክልሉን ሰላም ከማጽናት በተጓዳኝ ለሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በተለይ ገበያን በማረጋጋት የኑሮ ውድነቱን ማቃለል እንዲቻል የገበያ ማዕከላትን የማስፋፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢብራሂም መሀመድ(ዶ/ር) ቀደም ሲል ሸማችና አምራቹን የሚያገናኙ የገበያ ማዕከላት በስፋት ባለመኖራቸው የንግድ ስርዓቱ ለህገ ወጥ ተግባራት የተጋለጠ ነበር ብለዋል። ይህን ችግር ለመቅረፍም በተለያዩ አካባቢዎች የገበያ ማዕከላት ተገንብተው ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቁመው በቅርቡ ወደ ሥራ የገባው የደሴ ገበያ ማዕከልም ውጤታማ ሆኖ መቀጠሉን አንስተዋል። ዘንድሮም ክልሉ ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ መድቦ የገበያ ማዕከላትን ለማስፋፋትና ደረጃቸውን ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል። የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መሀመድአሚን የሱፉ በበኩላቸው፣ በማዕከሉ የኢንዱስትሪ እና የግብርና ምርቶች ለሕብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ይቀርባሉ ነው ያሉት። በምርቃቱ የፌዴራል፣ ከክልሎች የተውጣጡ የንግዱ ዘርፍ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በሸገር ከተማ አስተዳደር በበጋ መስኖ ከ41 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ዘር ተሸፍኗል
Jan 21, 2026 41
ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ አስተዳደር በበጋ መስኖ ከ41 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እርሻ በስንዴ ዘር መሸፈኑን የከተማው ግብርና ፅሕፈት ቤት ገለጸ። በሸገር ከተማ አስተዳደር የከተማ ግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ ደረጀ በቀለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ በከተማ አስተዳደሩ በበጋ መስኖ እየተከናወነ ያለው የስንዴ ልማት ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው፣ ግብርናውን የሚያዘመኑ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። በ2018 ምርት ዘመን በከተማ አስተዳደሩ ባሉ 12 ክፍለ ከተሞች የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ነው የተናገሩት። በመስኖ ስንዴ ልማቱ አርሶ አደሩ ተጨባጭ ውጤት እያገኘ በመሆኑ የሥራ ተነሳሽነቱ መጨመሩንም አመልክተዋል። በዘንድሮ ምርት ዘመን ከ41 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በበጋ ስንዴ በዘር መሸፈኑንና ሰብሉ የፀረ አረም ኬሚካሎች ርጭትን ጨምሮ እየተደረገ ባለው እንክብካቤ ቡቃያው የተሻለ ቁመና ላይ መገኘቱን ገልጸዋል። በዚህም ከ2 ነጥብ 4 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አቶ ደረጀ በቀለ አስታውቀዋል። ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በማህበራት በኩል የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በወቅቱ ከማቅረብ ጎን ለጎን አርሶ አደሩ የመሬት ለምነትን ለመጨመር የተፈጥሮ ማዳበሪያ በሰፊው አዘጋጅተው እንዲጠቀሙ መደረጉን ጠቁመዋል። እንዲሁም በዘርፉ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና መሰጠቱንና ሙያዊ ክትትልና ድጋፍ መደረጉንም አንስተዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢንስቲትዩቱ የመኖ እጥረትን ለመፍታት የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ ሊያጠናክር ይገባል
Jan 21, 2026 17
አዳማ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የመኖ እጥረትን ለመፍታትና የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ ሊያጠናክር እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። የቋሚ ኮሚቴው አመራሮችና አባላት በአዳማ ከተማ በሚገኘው የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምርምር ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ አድርገዋል። በዚህ ጊዜ በምክር ቤቱ የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፤ ኢንስቲትዩቱ የህብረተሰቡን ችግር በተጨባጭ መፍታት የሚችሉ ምርምሮች ለማከናወን እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀዋል። ደረቅ ቆሻሻን ወደ እንስሳት መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለመለወጥ የሚያስችል የፈጠራ ቴክኖሎጂ እውን ማድረጉ የዚህ ማሳያ መሆኑን በመጥቀስ። በገጠርም ይሁን በከተማ በዶሮና ዓሳ እርባታ የተሰማሩ ወጣቶችና አርሶ አደሮች መኖን በቀላሉ በቤታቸው እንዲያዘጋጁ ድጋፍ በማድረግ የመኖ እጥረትን ለመፍታት የኢንስቲትዩቱ ሚና ወሳኝ መሆኑንም ነው ያብራሩት። ኢንስቲትዩቱ ጠቃሚ የምርምር ውጤቶችን በማስፋፋት በባዮ ኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ ሚናውን የበለጠ እንዲያጎላም ጠይቀዋል። መኖን በአገር ውስጥ ማምረት የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግ መሆኑን ጠቅሰው፣ ኢንስቲትዩቱ በዚህ ረገድ የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል። የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ ፍሬው ታፈሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ስምንት ወራት ቆሻሻን ወደ ከፍተኛ ፕሮቲን ያለው የእንስሳት መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ የሚቀይር “ነብሳት” የተሰኘ ፕሮጀክት በመቅረፅ ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል። ቴክኖሎጂው ፍራፍሬን ጨምሮ የግብርናና የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶችን በመፍጨትና በማብላላት ወደ መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ የሚቀይር መሆኑን አስረድተዋል። አሁን ላይ በሳምንት 10 ኩንታል የዶሮ መኖ በማምረት በአዳማ ሰርቶ ማሳያና የስልጠና ጣቢያ የዶሮ እርባታ መጀመሩን ገልጸዋል። የዶሮ መኖን ከተረፈ ምርት የማግኘት፣ የማላመድና የማሳደግ ተግባራትን ወደ ተጠቃሚው ለማሸጋገር በሂደት ላይ መሆኑን አመልክተዋል።
ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለፋይናንስ ተቋማት የደንበኞች አገልግሎትን ለማፋጠንና ደህንነቱን ለማስጠበቅ ትልቅ እገዛ ያደርጋል
Jan 21, 2026 51
ጭሮ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፡- ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የፋይናንስ ተቋማት ደንበኞችን መረጃ አያያዝ ለማዘመን፣ ፈጣንና ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ተገለጸ። ኢዜአ በጭሮ ከተማ ከሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች ጋር በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት ላይ ቆይታ አድርጓል። የስራ ሀላፊዎቹ እንዳሉት ዲጂታል መታወቂያው የደንበኞች የዓይን፣ የፊት ገፅታና አሻራ በኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ በመያዝ አንድ ሰው ወጥ መረጃን ለመያዝ ከማጭበርበር የፀዳ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የጭሮ ኦዳ ቡልቱም ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ በላይ የሗላሸት እንዳሉት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በሐሰተኛ መታወቂያ የሚፈጸሙ የማጭበርበር ተግባራትን ለመከላከል ያስችላል። የዲጂታል መታወቂያ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ መረጃ መያዙ ተገልጋዩ አንድ ማንነት እንዲኖረው በማድረጉ ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ተናግረዋል። የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባንኩ አዲስ ለጀመረው የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጠን የማሻሻል ስራን የሚያቀላጥፍ መሆኑንም ጠቁመዋል። በአዋሽ ባንክ የጭሮ ቅርንጫፍ የደንበኞች አገልግሎት እና ኦፕሬሽን ስራ አስከያጅ አቶ ቴዎድሮስ ሰለሞን በበኩላቸው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ደንበኞችንና ባንኮች በተሟላ መልኩ እንዲተዋወቁ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያቀላጥፍ ነው። ደንበኛው በአንድ የፋይዳ ቁጥር ብቻ በመመዝገቡ ባንኮች የብድር አገልግሎት ሲሰጡ ደንበኞቻቸውን በሚገባ እንዲያውቁና የብድር ክትትሉን በተገቢው መልኩ እንዲያከናውኑ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል። የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በፋይናንስ ተቋማት ውስጥ እየተተገበረ ያለውን ከወረቀት ነፃ አገልግሎት ለማቀላጠፍ የሚያግዝ ነውም ብለዋል። በኢትዮ ቴሌኮም የጭሮ ማዕከል ሽያጭ ባለሙያ አቶ ተንኮሉ በቀለ በበኩላቸው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የአንድ ሰው መረጃን ወጥነት ባለው መንገድ በመመዝገብ ፈጣንና ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ የሚያሰፍን መሆኑን ጠቁመዋል።
መተግበሪያው አገልግሎትን ለማቀላጠፍና ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከል ትልቅ ፋይዳ አለው
Jan 20, 2026 119
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይፋ ያደረገው መተግበሪያ ዳያስፖራው ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 'CBE Connect Digital Wallet' የተሰኘ ከውጭ ሀገር ገንዘብ ለመላክ የሚያስችል አዲስ መተግበሪያ ስራ አስጀምሯል። የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ላይ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ባንኩ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በስኬት መሻገሩን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ለሚደረገው ጉዞ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ ዛሬ ይፋ የተደረገው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዲያስፖራው ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ ከማስቻሉም ባለፈ፣ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከልና የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ግኝት ለማሳደግ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት ተወካይና የኮርፖሬት አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ኤፍሬም መኩሪያ በበኩላቸው፤ ባንኩ በየወቅቱ አሰራሩን በማዘመን ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ባንኩ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት ላይ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። ስራ ላይ የዋለው መተግበሪያ የባንኩን የዲጂታል ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ጠቅሰው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ደንበኞችን ይበልጥ የሚያስተሳስርና የሐዋላ ሂደትን የሚያቀላጥፍ መሆኑን ተናግረዋል። መተግበሪያው በኢትዮጵያ የፋይናንስ ስርዓት ባለው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን መተግበሪያውን ከንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ያበለጸገው የስታር ፔይ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በሱፍቃድ ጌታቸው ገልጸዋል። መንግስት ለቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የፈጠረው ምቹ ሁኔታ መሰል ፈጠራዎች እንዲበራከቱ ማድረጉን ጠቅሰው፣ በቀጣይም ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለማበልጸግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና የዲጂታል ክህሎት እንድናጎለብት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮልናል
Jan 20, 2026 140
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና ከዘመኑ ጋር አብረን መራመድ የሚያስችለንን የዲጂታል ክህሎት እንድናጎለብት ምቹ ሁኔታን ፈጥሮልናል ሲሉ በመዲናዋ የኮደርስ ሰልጣኞች ገለጹ። ወጣቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎታቸውንና እውቀታቸውን እንዲያዳብሩ መንግስት የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መርሃ ግብር ዘርግቶ ብዙዎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ ኢዜአ ስልጠናውን በመውሰድ ተጠቃሚ የሆኑ ወጣቶችንና የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበርን አነጋግሯል። ማህበሩ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር ወጣቶች የዲጂታል እውቀታቸውን እንዲያሳድጉ የሚያስችል ስልጠና እንዲወስዱ እያገዘ እንደሚገኝም አስታውቋል። ወጣት ደረጄ ማሞ ማህበሩ የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የምንወስድበትን ምቹ ሁኔታን ፈጥሮልናል ብሏል፡፡ በማህበሩ እገዛ የዲጂታል ክህሎቱን ለማሳደግ የሚያግዘውን የኮደርስ ስልጠና በመውሰድ ራሱን ለማሻሻል መዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡ በዚህም ከኮደርስ መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ የሆነውን ዌብ ፕሮግራሚንግ በመምረጥ ስልጠና እየወሰደ እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ህይወት ገብረእግዚአብሄር በበኩሏ ከኢትዮ ኮደርስ የስልጠና አይነቶች አንዱ የሆነውን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መውሰዷን ገልጻለች። ስልጠናው የዲጂታል ክህሎቷን ለማሳደገ አቅም እየፈጠራላት መሆኑንና ይህንንም በእለት ከእለት የስራ እንቅስቃሴዋ ጥቅም ላይ ለማዋል ጥረት እያደረገች መሆኑን ተናግራለች። በርካታ ሀገራትና ግለሰቦች በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ስራዎቻቸውን እያከናወኑ መሆኑን የገለጸው ፋሲል ጉልላት እሱም ራሱን በቴክኖሎጂ ለማብቃት የአንድሮይድ የኮደርስ ስልጠና እየወሰደ መሆኑን ተናግሯል። ወጣቶች ያለንን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎትና እውቀት ለማዳበር እንደ ሀገር የሚፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎች ልንጠቀም ይገባል ብሏል። የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወጣት በረከት ቢርቢርሳ በበኩሉ፤ ወጣቶች የስራ እድል ፈጣሪና ተጠቃሚ እንዲሆኑ የኮደርስ ስልጠና ሚናው የጎላ እንደሆነ ተናግሯል። ማህበሩ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር ወጣቶች ስለ ኮደርስ ስልጠና ግንዛቤ እንዲጨብጡ ማድረጉን ጠቅሶ፤ አሁን ላይ 81ሺህ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እየወሰዱ እንደሚገኙ ጠቁሟል።
ስፖርት
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና ሸገር ከተማ አቻ ተለያዩ
Jan 21, 2026 28
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና ሸገር ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሄኖክ አዱኛ በ22ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠራት ግብ ሸገር ከተማ መሪ ሆኗል። ሐዋሳ ከተማ ከነገሌ አርሲ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው ጋናዊው ኮንኮኒ ሀፊዝ በ33ኛው ለወልዋሎ የአቻነቷን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ቡልቻ ሹራ ከሸገር ከተማ፣ ሰመረ ሀፍታይ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥተዋል። ሸገር ከተማ በ16 ነጥብ ደረጃውን ከ17ኛ ወደ 16ኛ ከፍ በማድረግ ከወራጅ ቀጠና ወጥቷል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ13 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሁለቱ ቡድኖች በተመሳሳይ ያለፉትን ሰባት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻሉም።
በሻምፒዮንስ ሊጉ ባየር ሙኒክ ከዩኒየን ሴይንት-ጂሎይስ ጋር ይጫወታል
Jan 21, 2026 55
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ዘጠኝ ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በአሊያንዝ አሬና ስታዲየም ምሽት አምስት ሰዓት ላይ ባየር ሙኒክ ከዩኒየን ሴይንት-ጂሎይስ ጋር ይጫወታል። የስድስት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ባየር ሙኒክ በ15 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። በሻምፒዮንስ ሊጉ ኢንተር ሚላን ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው አርሰናል በሻምፒዮንስ ሊጉ ጥሎ ማለፍ የገባ የመጀመሪያ ቡድን ሆኗል በውድድሩ ላይ የመጀመሪያ ተሳትፎውን እያደረገ የሚገኘው ዩኒየን ሴይንት-ጂሎይስ በስድስት ነጥብ 30ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱ ክለቦች በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ሲገናኙ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ባየር ሙኒክ ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ ግምት ያገኘ ሲሆን፤ ሶስት ነጥብ ማግኘት ወደ ጥሎ ማለፍ የመግባት እድሉን ያሰፋዋል። በሌሎች መርሐ-ግብሮች ማርሴይ ከሊቨርፑል፣ ቼልሲ ከፓፎስ፣ ስላቪያ ፕራግ ከባርሴሎና፣ ጁቬንቱስ ከቤኔፊካ፣ ኒውካስትል ዩናይትድ ከፒኤስቪ አይንድሆቨን እና አትላንታ ከአትሌቲኮ ቢልባኦ በተመሳሳይ ምሽት አምስት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በሻምፒዮንስ ሊጉ ማንችስተር ሲቲ በቦዶ ግሊምት ያልተጠበቀ ሽንፈት አስተናገደ ጋላታሳራይ ከአትሌቲኮ ማድሪድ እና ካራባግ ከኢንትራክት ፍራንክፈርት በተመሳሳይ ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ ይጫወታሉ።
ሐዋሳ ከተማ ከነገሌ አርሲ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Jan 21, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 13 /2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት 12 ሠዓት ሐዋሳ ከተማ ከነገሌ አርሲ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሐዋሳ ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው 15 ጨዋታዎች በሰባቱ አሸንፎ በአራቱ ተሸንፎ በአራቱ አቻ ወጥቷል። በ15ቱ ጨዋታዎች 16 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 10 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ25 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ነገሌ አርሲ በሊጉ 15 ጨዋታዎች አከናውኖ ሰባት ጊዜ ድል ሲቀናው በሶስቱ ተሸንፏል። አምስት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። 17 ግቦችን ሲያስቆጥር 10 ጎሎችን አስተናግዷል። አዲስ አዳጊው ነገሌ አርሲ በ26 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታው ሁለቱ ክለቦች ከ15ኛ ሳምንት የአቻ ውጤታቸው በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። በሌላኛው መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአዳማ ከተማ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እስከ አሁን በሊጉ ማሸነፍ የቻለው ጨዋታ ብዛት ሶስት ብቻ ነው። አራት ጊዜ ሲሸነፍ ስምንት ጊዜ አቻ ወጥቷል። 17 ግቦችን ሲያስቆጥር በተመሳሳይ 17 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ17 ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው አዳማ ከተማ በበኩሉ 15 ጨዋታዎችን አድርጎ አምስት ጊዜ ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። በስምንት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 11 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 9 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አዳማ ከተማ በ23 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ15ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር በኢትዮ ኤሌክትሪክ የ2 ለ1 ሽንፈት አስተናግዷል። አዳማ ከተማ ባለፉት ሶስት የሊጉ ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ምድረ ገነት ሽሬ ከአርባ ምንጭ ከተማ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። ምድረ ገነት ሽሬ በ17 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። አርባ ምንጭ ከተማ በስምንት ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ምድረ ገነት ሽሬ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል። አርባ ምንጭ ከተማ በሊጉ ምንም ጨዋታ ያላሸነፈ ብቸኛው ክለብ ነው። ጨዋታው ምድረ ገነት ሽሬ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ፣ አርባ ምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ሶስት ነጥቡን ለማግኘት የሚያደርጉት ነው። ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከሸገር ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። በደረጃ ሰንጠረዡ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ12 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሸገር ከተማ በ15 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሁለቱም ቡድኖች በተመሳሳይ ባለፉት ስድስት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻሉም። ሶስት ነጥብ ለሁለቱም ወሳኝ ነው።
አርሰናል በሻምፒዮንስ ሊጉ ጥሎ ማለፍ የገባ የመጀመሪያ ቡድን ሆኗል
Jan 21, 2026 61
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተጠባቂ መርሐ-ግብር አርሰናል ኢንተር ሚላንን 3 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በሳንሲሮ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ጋብርኤል ጄሱስ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ተቀይሮ የገባው ቪክቶር ዮኬሬስ ቀሪዋን ጎል ከመረብ አሳርፏል። ፔታር ሱቺች ለኢንተር ሚላን ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በ21 ነጥብ አንድ ጨዋታ እየቀረው ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለ የመጀመሪያ ቡድን ሆኗል። አርሰናል በዘንድሮው ሻምፒዮንስ ሊግ ሁሉንም ጨዋታዎች ያሸነፈ ብቸኛው ክለብ ነው። በውድድሩ ሶስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢንተር ሚላን በ12 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። በሌሎች መርሐ-ግብሮች የ15 ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ሪያል ማድሪድ ሞናኮን በሜዳው 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል። ኪሊያን ምባፔ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ፍራንኮ ማስታንቱኖ፣ ቪኒሺየስ ጁኒየር፣ ጁድ ቤሊንግሃም እና የሞናኮው ቲሎ ኬህረር በራሱ ላይ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ጆርዳን ቴዜ ለሞናኮ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ሪያል ማድሪድ በ15 ነጥብ ሶስተኛ፣ ሞናኮ በዘጠኝ ነጥብ 20ኛ ደረጃን ይዘዋል። ስፖርቲንግ ሊዝበን የወቅቱን የዋንጫ ባለቤት ፒኤስጂን ሳይጠበቅ 2 ለ 1 አሸንፏል። ሉዊስ ሱዋሬዝ ለስፖርቲንግ ሊዝበን ሁለቱን ግቦች ሲያስቆጥር ክቪቻ ክቫርትስኬሊያ ለፒኤስጂ ብቸኛውን ጎል ከመረብ አሳርፏል። ቶተንሃም ሆትስፐርስ ቦሩሲያ ዶርትሙንድን 2 ለ 0 ሲረታ ክርስቲያን ሮሜሮ እና ዶምኒክ ሶላንኬ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። የቦሩሲያ ዶርትሙንዱ ዳንኤል ስቬንሰን በ24ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ኮፐንሃገን እና ናፖሊ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ጆርዳን ላርሰን ለኮፐንሃገን፣ ስኮት ማክቶሚናይ ለናፖሊ ግቦቹን አስቆጥረዋል። የኮፐንሃገኑ ቶማስ ዴላኒ በ35ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ኦሎምፒያኮስ ባየር ሌቨርኩሰንን 2 ለ 0 ሲረታ አያክስ ቪያሪያልን 2 ለ 1 አሸንፏል።
አካባቢ ጥበቃ
የተፋሰስ ልማት የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሰረት ሆኗል- ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Jan 21, 2026 53
ሀዋሳ፣ጥር 13/2018 (ኢዜአ):-በሲዳማ ክልል የተፋሰስ ልማት ሥራ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሰረት መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ ክልል አቀፉን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀዌላ ወረዳ ዱለቻ ጠዌራኮ ቀበሌ አስጀምረዋል። አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርታማነት እንዲጨምር አድርጓል። የተፋሰስ ልማት ሥራው የተጎዳ መሬት እንዲያገግም በማድረግ የአፈር ለምነትን ከመጠበቅ ባሻገር ለወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱንም ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም በጎርፍ ምክንያት የአፈር መሸርሸር ሲከሰት እንደነበር አስታውሰው፣ በተፋሰስ ልማት ሥራው በለሙ አካባቢዎች የእንስሳት መኖን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። በተፋሰስ ልማት ሥራው የተገኙ ውጤታማ ሥራዎችን በማስቀጠል አረንጓዴና ለኑሮ ምቹ ስነምህዳር የመፍጠር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፋኖሴ መኮንን በበኩላቸው፣ ባለፉት ዓመታት እንደሃገር በተከናወነ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ 33 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሚጠጋ መሬት መልማቱን ተናግረዋል፡፡ በዚህም የአፈር ለምነትን በመጠበቅ የግብርና ምርታማነትን የማሳደግ፣ የውሃ አማራጮችን የማስፋትና በለሙ ተፋሰሶች የስራ ዕድል በመፍጠር ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በሲዳማ ክልል በ2018 በተለዩ 678 ንኡስ ተፋሰሶች የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በማከናወን ከ147 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የገለጹት ደግሞ የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ ናቸው። ለአንድ ወር በሚቆየው የተፋስስ ልማት ሥራ ተዳፋታማ በሆነ አካባቢዎች ለሚከናወን የጠረጴዛማ እርከን ስራና በእርሻ ማሳ ውስጥ ያለውን ባህር ዛፍ በመንቀል በትኩረት እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ሥራዎች የአፈር መከላትን መቀነስ፣ የውሃ አማራጮችን የማስፋትና ምርት የማይሰጡ አካባቢዎችን ወደ ምርት በማስገባት ዓመታዊ የሰብል መሬት ሽፋን ለማሳደግ መሰራቱን ገልጸዋል። በቀበሌው ከዚህ ቀደም በለማ ተፋሰስ የሥራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል ወጣት እንድሪያስ ኢዩኤልና ሰለሞን ዳንኤል በተፋስስ ልማት በለሙ አካባቢዎች የሥራ እድል እንደተፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡ በአካባቢው በለማ ተፋሰስ ላይ ለአምስት ተደራጅተው በመንግስት በተመቻቸላቸው የገንዘብ ብድር በንብ በማነብ ሥራ ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በመርሃግብሩ ላይ የሲዳማ ክልል አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ሥራ ሃላፊዎች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ከፍሎች ተሳትፈዋል፡፡ በዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ሥራ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይሳተፋል ተብሏል።
የተፈጥሮ ፀጋን የማልማትና የመጠበቅ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
Jan 21, 2026 93
ካራት፤ ጥር 13/2018 (ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተፈጥሮ ፀጋን በማልማትና በመጠበቅ ለትውልድ ምቹ ሥነ ምህዳር ለማውረስ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠናከር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። ክልል አቀፍ የ2018 በጀት ዓመት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትና የበልግ አዝመራ ንቅናቄ መርሃ ግብር ዛሬ በኮንሶ ዞን በይፋ ተጀምሯል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የክልሉን የተፈጥሮ ፀጋ በማልማት ለትውልዱ ምቹ ስነ ምህዳር ለማውረስ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ እየተከናወነ ነው። ባለፉት ዓመታት በቅንጅት በተሰሩ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ሥራዎችም ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ የተራቆቱ ተራራዎችን በማልማት ከስጋት ወደ ሀብት ምንጭነት ለመለወጥ መቻሉን ተናግረዋል። በዘንድሮ የተፋሰስ ልማት ሥራም የኮንሶዎችን የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ባህልን በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ለማስፋፋት ልዩ ትኩረት መሰጠቱንም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። በክልሉ ያለውን የተፈጥሮ ሀብት በማልማትና በመጠበቅ ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ለትውልዱ ምቹ ሥነ ምህዳር ለማውረስ የተጀመረው ሥራ በቀጣይም ይጠናከራል ብለዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) የዘንድሮው የተፋሰስ ልማት በ159 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እንደሚከናወን ገልጸዋል። በዚህም 1ሺህ 384 የተለያዩ ቦታዎች ላይ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል። በተፋሰስ የለሙ አካባቢዎችን በስነአካላዊና ስነ ህይወታዊ ሥራዎች ፍራፍሬና የእንስሳት መኖ በማልማት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተጀመረውን ጉዞ ለማሳካት ይሰራል ሲሉም አመልክተዋል። እንደኃላፊው ገለጻ በክልሉ ባለፉት ስድስት ዓመታት የተፋሰስ ልማት ሥራ በተከናወነባቸው አካባቢዎች ከ164 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል። የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ገሌቦ ጎልቶሞ በበኩላቸው በዞኑ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራው የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት እያሳደገው መምጣቱን ነው የተናገሩት። ኮንሶዎች ከ500 ዓመታት በፊት የጀመሩት የእርከን ሥራ ለምርትና ምርታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም አመልክተዋል። በዞኑ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት፣ በመንከባከብና በአግባቡ በመጠቀም የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ባህልን በማሳደግ ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ የበኩላችንን እየተወጣን እንገኛለን ያሉት ደግሞ የኮንሶ ዞን አርሶ አደር ካፖሌ ገድሻ ናቸው። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ለአንድ ወር በሚካሄደው የተፋሰስ ልማት ሥራ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተፋሰስ ልማትና የበልግ አዝመራ ንቅናቄ መርሃ ግብር ላይ የክልሉና የዞን ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ የኮንሶ ዞን ነዋሪዎችና ሌሎችም ተሳትፈዋል።
የተፋሰስ ልማት ሥራ ለምርታማነት መጨመር ከፍተኛ እገዛ አድርጓል
Jan 20, 2026 122
መቱ፤ ጥር 12/2018 (ኢዜአ)፡- የተፋሰስ ልማት ሥራ ለምርታማነት መጨመርና ለተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን የቡኖ በደሌና የኢሉባቦር ዞኖች አርሶ አደሮች ተናገሩ። በቡኖ በደሌ ዞን የዳቦ ሐና ወረዳ ነዋሪዎች አርሶ አደር ዲንቃ ገቢ እና ታሪኩ አብዲሳ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ምርታማነት እንዲጨምር ከፍተኛ እገዛ አድርጓል። በተጨማሪም እየተመናመኑ የነበሩ የደንና የውኃ ሀብቶች እንዲመለሱ ማድረጉን ተናግረዋል። የተፋሰስ ልማት ሥራ የተጎዱ መሬቶች እንዲያገግሙና ምርታማነታቸው እንዲጨምር ማድረጉን የተናገሩት ደግሞ በኢሉአባቦር ዞን የሁሩሙ ወረዳ ነዋሪ አርሶአደሮች ተካልኝ ታደገ እና ዓለማየሁ በቀለ ናቸው። የተፋስ ልማት የተከናወነባቸው አካባቢዎችን ከሰውና ከእንስሳት ንኪኪ በመጠበቅ ለመኖ ልማት ብሎም ለንብ ማነብ ሥራ እያዋሏቸው መሆኑንም ጠቁመዋል። ቀደም ሲል ከተከናወነ የተፋሰስ ልማት የተገኘውን ተጠቃሚነት በመገንዘብ፤ በቀጣይም ሥራውን በባለቤትነት አጠናክረው ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የቡኖ በደሌ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አማን ደኑ በበኩላቸው፤ የተፋሰስ ልማት ሥራ በአርሶ አደሩ ዘንድ መደበኛ ተግባር ሆኖ እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል። የዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመከላከል፣ ምርታማነትን ለማሳደግና የተፈጥሮ ሀብትን ለመጠበቅ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ወሳኝ ነው ያሉት ደግሞ የኢሉአባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቻላቸው አዱኛ ናቸው። ለሁለት ወራት የሚቆይ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ በዞኖቹ በ479 ተፋሰሶች ላይ እየተከናወነ ይገኛል።
በብሔረሰብ አሥተዳደሩ በሞዴል መንደሮች የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራ ይከናወናል
Jan 16, 2026 113
ሰቆጣ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር በሰባት ሞዴል መንደሮች የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታወቀ። በአሥተዳደሩ የገጠር ኮሪደር ልማትን ለማሳካት ያለመ የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በሰቆጣ ከተማ ተካሂዷል። የብሔረሰብ አሥተዳደሩ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የመንገድ መምሪያ ኃላፊ ፀጋው እሸቴ በዚሁ ወቅት፤ ከዚህ ወር መጨረሻ ጀምሮ ወደ ተግባር የሚገባው የገጠር ኮሪደር ልማት በሕዝብ ተሳትፎ ታጅቦ ይከናወናል ብለዋል። በሁሉም ወረዳዎች ሰባት ሞዴል መንደሮችን በመለየት የገጠር ኮሪደር ልማት እንደሚከናወን የገለጹት ደግሞ የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አዲስ ወልዴ ናቸው። በገጠር ኮሪደር ልማት ቅንጅታዊ አሠራርን በመከተል የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል እንደሚሠራ ጠቁመዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የኢጋድ የ40 ዓመታት ጉዞ፤ ከድርቅ አደጋ ምላሽ ሰጪነት እስከ ቀጣናዊ ትስስር ተዋናይነት
Jan 21, 2026 115
በሙሴ መለሰ ምስራቅ አፍሪካ በአፍሪካ አህጉር በየጊዜው ከፍተኛ ለውጥ የሚያስተናግድ እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ቀጣና ነው። ከ300 ሚሊየን በላይ ህዝብ የሚኖርበት ይህ ቀጣና ከፍተኛ የሰው ሀብት ያለው ሲሆን ፈጣን የወጣት ህዝብ እድገት እና የገበያ ተደራሽነት መስፋት እየታየበት ይገኛል። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የምስራቅ አፍሪካ አጠቃላይ ዓመታዊ ጥቅል ምርት(ጂዲፒ) እ.አ.አ በ2025 598 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር መድረሱን ገልጿል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ያሉ ሀገራት የሚገኙበት ቀጣና ነው ምስራቅ አፍሪካ። ምስራቅ አፍሪካ ግብርና፣ ቁም እንስሳት፣ ኢነርጂ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ንግድ፣ ትራንስፖርት፣ የኢኮኖሚ ኮሪደሮች እና በፍጥነት እያደገ የመጣው ዲጂታል ኢኮኖሚ እምቅ የኢኮኖሚ አቅሞቿ ናቸው። ከመልክዐ ምድራዊ አቀማመጥ አንጻርም የኢትዮጵያ ከፍታማ ስፍራዎች፣ የታላላቅ ሀይቆች ተፋሰስ እና የአፍሪካ ቀንድ ዝቅተኛ ቦታዎች ይጠቀሳሉ። ከቀይ ባህር እስከ ህንድ ውቅያኖስ ምስራቅ አፍሪካን የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የዓለም የማሪታይም ንግድ መተላለፊያ መስመሮች ይገናኙባታል። ይህ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ ምስራቅ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ንግድ፣ ሎጂስቲክስ እና ጂኦ ፖለቲካ ውስጥ ያላትን ሚና አሳድጓል። ቀጣናው ለመረጋገት እና ለትብብር ያለው ጠቀሜታም በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ለብዙ ክፍለ ዘመናት በምስራቅ አፍሪካ የሚገኙ የተለያዩ ማህበረሰቦች በንግድ፣ በፍልሰት እና የባህል ትስስር ተጋምደዋል። በዘመናዊው ዓለም ይህ ታሪካዊ ትስስር ለቀጣናዊ ትስስር ጠንካራ አስተዋጽኦ ያለው ነው። በሀገራት በጋራ የሚገነቡ መሰረተ ልማቶች፣ የተሳናሰኑ ፖሊሲዎች እና የሰዎችና እቃዎች ነጻ ዝውውር የኢኮኖሚ እድገት እና አጠቃላይ ልማትን የሚያሳልጥ ነው። ቀጣናዊ ትስስር የተበታተነ ገበያ ወደ አንድ ማዕቀፍ ለማምጣት፣ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ዜጎች በተለይም ወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አኳያ አስተዋጽኦወ ቁልፍ ነው። ምስራቅ አፍሪካ እንደ እድሎቹ ሁሉ በርካታ ፈተናዎች ያሉበት ቀጣና ነው። በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚፈጠረው ድርቅ እና ጎርፍ፣ ግጭት፣ መፈናቀል እና የልማት ተደራሽነት ፍትሃዊ አለመሆን በዋናነት የሚነሱ ጉዳዮች ናቸው። እነዚህ ድንበር ተሻጋሪ ፈተናዎች ከተናጠል ይልቅ የጋራ የተግባር ምላሽ ይፈልጋሉ። ፈተናዎችን ከግምት በማስገባት በቀጣናው በተደጋጋሚ ለሚከሰተው ድርቅ እና የከባቢ አየር ችግር የተቀናጀ ምላሽ መስጠት የሚያስችለው ተቋማዊ ማዕቀፍ ከ40 ዓመታት በፊት ወደ ስራ ገባ። ይህ ተቋም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ነው። የኢጋድ መቋቋም እርሾ በወቅቱ በቀጣናው ያጋጥሙ የነበሩ ቀውሶች ናቸው። እ.አ.አ በ1980ዎቹ መጀመሪያ በቀጣናው የነበረው ድርቅ እና ረሃብ የብዙ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈ ሲሆን ይህም ቀጣናው ለአየር ንብረት ለውጥ ያለውን ተጋላጭነት በግልጽ የሚያሳይ ነው። አደጋዎቹ ድንበር ተሻጋሪ በመሆናቸው የተቀናጀ የጋራ ምላሽ የሚፈልጉ ናቸው። ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን እና ዩጋንዳ ለአንገብጋቢው ቀጣናዊ ጉዳይ ምላሽ በመስጠት ኢጋድን እ.አ.አ በ1986 አቋቋሙ። ኢጋድ በወቅቱ ሲቋቋም ዋነኛ የስራ ድርሻው የነበረው ድርቅ፣ በረሃማነት እና ሁለቱ የሚያደርሷቸውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽእኖዎችን ለመከላከል የሚደረጉ ቀጣናዊ ጥረቶችን ማስተባበር ነው። ይሁንና የከባቢ አየር ፈተናዎቹ ከፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ግጭት እና ካለመልማት ጋር ጥልቅ ቁርኝት ያላቸው መሆኑ አድማሱ የሰፋ ግብ ያለው ቀጣናዊ ተቋምን መፍጠር እንደሚያስፈልግ በወቅቱ ይነሳ ነበር። በዚሁ መሰረት ኢጋድ እ.አ.አ በ1996 በድጋሚ አደረጃጀቱ ተስተካክሎና የስራ ድርሻው ሰፍቶ እንደገና ተቋቋመ። ከድርቅ እና ከባቢ አየር ጉዳዮች በመሻገር ኢጋድ ሰላም እና ደህንነትን ማረጋገጥ፣ የኢኮኖሚ ትብብር እና ትስስር እንዲሁም ቀጣናዊ ትስስርን ማጎልበት የተቋሙ ቁልፍ የትኩረት መስኮች ሆነዋል። የኢጋድ ዋና መቀመጫ ጅቡቲ ነው። የሰፋው የስራ ድርሻ ኢጋድን በአፍሪካ ቀንድ የምክክር፣ የውይይት እና የተቀናጀ ልማት የጋራ ማዕቀፍ እንዲሆን አድርጎታል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) እ.አ.አ በ2026 የተመሰረተበትን 40ኛ ዓመት እንደሚያከብር ከሰሞኑ አስታውቋል። ኢጋድ በአራት አስርት ዓመታት ውስጥ በስኬት ደረጃ ሊነሱ የሚችሉ ተግባራትን አከናውኗል። ከሰላም እና ደህንነት አንጻር ኢጋድ በቀጣናው ውስብስብ የሚባሉ ግጭቶች በእርቅ እና በውይይት እንዲፈቱ አስተዋጽኦ አድርጓል። ለዓመታት በሱዳን ሲካሄድ የነበረውን የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲያበቃ እ.አ.አ በ2005 ሁሉን አቀፍ የሰላም ስምምነት እንዲፈረም በሰላም ሂደት ውስጥ የድርሻውን ተወጥቷል። ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ደቡብ ሱዳን በህዝበ ውሳኔ ራሷን የቻለች ሀገር ሆናለች። ኢጋድ በሶማሊያ የሰላም ጥረቶች ቁልፍ ተዋናይ ነበር። በሶማሊያ የፖለቲካ እርቅ እና መረጋጋት እንዲፈጠር ሲከናወኑ በነበሩ ስራዎች ላይ ተሳትፎ አድርጓል። ቀጣናዊ ተቋሙ ባለው የእርቅ የስራ ክፍል ግጭቶች እንዳይከሰቱና ከተከሰቱም እንዲፈቱ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣም ይገኛል። ከተቋቋመበት የስራ ድርሻ አኳያ ኢጋድ በምግብ ደህንነት፣ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አደጋ ስጋት አስተዳደር ላይ ሰፋፊ ተግባራትን አከናውኗል። ለአብነትም የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያና ትግበራ ማዕከል (ICPAC) የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓቶችን በማጠናከር፣ በአየር ትንበያዎች እና የፖሊሲ ድጋፎች አማካኝነት አባል ሀገራት ለድርቅ እና ጎርፍ አደጋዎች ምላሽ እንዲሰጡ የድርሻውን እየተወጣ ይገኛል። ይህም ቀጣናዊ የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽን ለማጠናከርና የመንግስታትን አቅም ከመገንባት አኳያ ትልቅ ድርሻ እንደተወጣ ማዕከሉ ይገልጻል። ከኢኮኖሚ ትብብር እና ቀጣናዊ ትስስር አኳያም ኢጋድ ድንበር ተሻጋሪ ንግድ እንዲያድግ፣ መሰረተ ልማት እንዲስፋፋና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እንዲጠናከሩ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በትራንስፖርት ኮሪደሮች፣ በአርብቶ አደሮች እንቅስቃሴዎችና ቀጣናዊ ገበያዎች ላይ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ በአባል ሀገራት እንዲተገበር ከማድረግ ባለፈ ድጋፉን እየሰጠ ነው። ኢጋድ በቀጣናው ለንግድ እና ለእንቅስቃሴ የሆኑ መሰናክሎች እንዲቀንሱ አስተዋጽኦ አድርጓል። ኢጋድ ከፍልሰተኞች ና ተፈናቃዮች ጋር ያሉ ችግሮች እንዲፈቱና ጉዳዩ ከፈተና ባለፈ የልማት እድል እንደሆነ በማንሳት ሁሉን አቀፍ እይታ እንዲፈጠር እየሰራ ይገኛል። በአራት አስርት ዓመታት ውስጥ ኢጋድ ተቋማዊ አቅሙን በማጠናከርና አጋርነቱን በማስፋት ረገድ የተለያዩ ስራዎችን አከናውኗል። ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ከሌሎች ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር እየሰራ ነው። ተቋሙ በቴክኒካዊ እና ፖለቲካዊ ደረጃዎች ለአባል ሀገራት ቋሚ የምክክር ማዕቀፍ ሆኖ እያገለገለ ሲሆን ይህም በሀገራት መካከል የጋራ መተማመንና የጋራ መግባባት እንዲኖር ያለው አስተዋጽኦ ወሳኝ የሚባል ነው። የኢጋድ የ40 ዓመታት ጉዞ በስኬቶች ብቻ የታጀበ አይደለም። ቀጣናዊ ተቋሙ ከፍተኛ ፈተናዎችም አጋጥመውታል። የመጀመሪያው በተደጋጋሚ ጊዜ የሚቀሰቀሱ እና ዘላቂ መቋጫ ያላገኙ ግጭቶችና የፖለቲካ አለመረጋጋቶች ናቸው። ጉዳዮቹ የኢጋድን የእርቀ ሰላም ጥረቶች ፈተና ውስጥ ከተውታል። አንዳንድ ጊዜ በአባል ሀገራት መካከል ያሉ መከፋፈሎች ኢጋድ ቆራጥ ውሳኔ እንዳይወስን ሲገድበው ታይቷል። የፋይናንስና ተቋማዊ አቅም ውስነነቶች የኢጋድ የተለያዩ ማዕቀፎች ትግበራ ላይ መስተጓጎሎችን ፈጥረዋል። ኢጋድ ከውጭ አጋሮች የሚያገኘው ፈንድ ከራስ ዘላቂ የፋይናንስ አቅርቦት ጋር ማመጣጠን አለመቻል የተቋሙን የዘላቂነት እና የባለቤትነት ጉዳይ ላይ ተጽእኖ አሳድረዋል። የፖለቲካ ተንታኞች ተቋሙ ከአባል ሀገራቱ የሚያገኝውን ጨምሮ ገቢ እና የፋይናንስ ቅሙን የሚያጠናክርባቸውን መንገዶች በሚገባ ማየት እንዳለበት ይመክራሉ። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ሌላኛው የኢጋድ ፈተና ነው። በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ደጋግመው የሚከሰቱ ድርቆች እና የጎርፍ አደጋዎች በተቋማዊ ምላሽና አቅም ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድረዋል። ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት መስፋፋትና መፈናቀል ጫናዎቹ ይበልጥ እንዲበረቱ አድርገዋል። ቀጣናዊ ስምምነቶችና የአሰራር ማዕቀፎችን ወደ ተጨባጭ የሀገራት ትግበራ የማሸጋገር ጉዳይም ትኩረት እንደሚያሻውም ይነሳል። የሀገራት የሚለያዩ የትኩረት መስኮች እና አቅሞች በቀጣናዊ ማዕቀፎች ሂደትና ትግበራ ላይ የራሳቸውን ተጽእኖ ያሳድራሉ። 40 ዓመታትን ያስቆጠረው ኢጋድ በምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ትብብር ያለውን ወሳኝ ጠቀሜታ የሚያሳይ ህያው ተቋማዊ ምስክር ነው። ለድርቅ እና ረሃብ ምላሽ ከመስጠት በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት፣ አንድነት እና ልማት ቁልፍ ተዋናይነት ተሸጋግሯል። አንድነት እና የፖለቲካ ቁርጠኝነትን በኢጋድ አባል ሀገራት መካከል ማጠናከር ለቀጣናዊ የተግባር ምላሽና ለተቋሙ ዘላቂ ውጤታማነት ወሳኝ የሚባሉ ጉዳዮች ናቸው። የአባል ሀገራት የጋራ አንድነት የተረጋገጠበት ኢጋድ ለቀውሶች ምላሽ ከመስጠት ባለፈ ለጋራ ፍላጎቶች መሳካት ያለው ሚናም ያድጋል። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ግንባታና ዘላቂ ልማት ላይ ቀጣይነት ባለው መልኩ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ የኢጋድ የትኩረት አጀንዳ ሊሆን ይገባል። የኢጋድ የሰላም እና መረጋጋት ጥረቶች በሁሉን አቀፍ አስተዳደር፣ በወጣቶችና ሴቶች የነቃ ተሳትፎ እንዲሁም በዘላቂ የሀገር ግንባታ አካሄዶች ሊደገፍ እንደሚገባ የፖለቲካ ባለሙያዎች ምክረ ሀሳባችውን ያስቀምጣሉ። የልማት ፍላጎት አለመሟላት እና የኑሮ ውድነትን ለግጭቶች አበይት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን ከስር መሰረቱ መፍታት ለዘላቂ መረጋጋት ወሳኝ ነው። ኢጋድ የተጣለበትን ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር እውን የማድረግ ኃላፊነቱን የበለጠ ለመወጣት የመሰረተ ልማት ትስስሮች ማጠናከር፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እውን ማድረግና በቀጣናው በፍጥነት እያደገ ለመጣው ዜጋ የስራ ፈጠራና እድሎችን የሚያሰፉ ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶችን የማስፋት ስራ ላይ አበክሮ መስራት ይኖርበታል። ፈተናዎች እንዳሉ ሆነው የኢጋድ የ40 ዓመታት ጉዞ የሚያሳየው አንድ ግልጽ ሀቅ አለ። ይህም እውነታ የምስራቅ አፍሪካ መጻኢ ጊዜ እርስ በእርስ መተሳሰርና በትብብር መቆም እንደሆነ ነው። የተቋቋመበትን አላማ ዳግም ቃል ኪዳኑን በማደስ በቁርጠኝነት መስራት ከቻለ፣ ተቋማዊ አቅሙን በሚገባ ካጎለበተ፣ በሀገራት መካከል አጋርነትና ትብብርን ካጠናከረና የዲጂታል ዘመን በሚገባ በመዋጀት ከሰራ ኢጋድ ቀጣዩ ትውልድ ሰላማዊ፣ አይበገሬናና የበለጸገ ቀጣና እንዲረከብ በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና መጫወቱን መቀጠል ይችላል።
የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ትብብራቸውን ለማጽናት ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Jan 14, 2026 147
አዲስ አበባ፤ ጥር 6/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን በባለብዙ ወገን መድረኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አያኖ ኩኒሚትሱ ጋር በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ትብብር እንዳላቸው አውስተው በጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም (ቲካድ) ማዕቀፍ ያላቸውን ግንኙነት አንስተዋል። በዮካሃማ በነሃሔ ወር 2017 ዓ.ም የተካሄደው ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም(ቲካድ) በሁለቱ ወገኖች አጋርነት ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው መሆኑን አመልክተዋል። ውይይቱ የሁለትዮሽ ትብብሩን የበለጠ ማጠናከርን ያለመ ነው። ጃፓን ለአፍሪካ የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (African CDC) እያደረገች ያለው ድጋፍ እንዲሁም የአፍሪካ ዘላቂ እድገት እና ትስስር ለሚደግፉ የመሰረተ ልማት ስራዎች እያፈሰሰች ያለው መዋዕለ ንዋይ እያደገ መምጣቱ ተመላክቷል። የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አያኖ ኩኒሚትሱ ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም (ቲካድ) በስኬት መካሄዱን አድንቀዋል። 10ኛው ቲካድ በአፍሪካ እንዲካሄድ ጃፓን ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ጋር በቅርበት ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን አመልክተዋል። ሀገራቸው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና (AfCFTA) እና የአፍሪካ የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ፕሮግራም (ፒዳ) ጨምሮ የአፍሪካ ህብረት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ቁልፍ ኢኒሼቲቮች መደገፏን እንደምትቀጥል ገልጸዋል። በሌላ በኩል ሚኒስትር ዴኤታዋ በዓለም አስተዳደር ውስጥ እያደገ የመጣውን የአፍሪካ ሚና በማንሳት የአፍሪካ ህብረት በቡድን 20 ቋሚ አባል መሆኗ ትልቅ ሽግግር መሆኑን ተነግረዋል። ባለስልጣናቱ በአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን የከፍተኛ ደረጃ የምክክር መድረክ እና ቲካድ አማካኝነት ትብብራቸውን የበለጠ ለማጠናከር እና የባለብዙወገን ዲፕሎማሲ እንዲጸና በጋራ እንደሚሰሩ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን እ.አ.አ በ1993 አጋርነት መመስረታቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ። ሰላም እና ደህንነት፣ ኢኮኖሚ፣ ልማት፣ ንግድ፣ ጤና ፣ ግብርና፣ ቴክኖሎጂ እና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ከሁለቱ ወገኖች የትብብር መስኮች መካከል ይጠቀሳሉ።
ውኃ ለአፍሪካ የኅልውና ጉዳይ ነው - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Jan 12, 2026 244
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ ውኃ ሁሉንም ዘርፍ የሚነካ አህጉራዊ የኅልውና ጉዳይ መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የሕብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ስብሰባው"ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሐሳብ የሚደረግ ነው። በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ፣ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት ትኩረቱን ያደረገው በውኃ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ውኃ በሁሉም አይነት እጅጉን ወሳኝ የሆነ ሀብት እና የኅልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ አህጉራዊ ግቦቹን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አስገንዝበዋል። በብራዚል ቤለም የተካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) ትኩረት ከተሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል አንዱ መሆኑንም አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በምታዘጋጀው 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ውኃ አንዱ አጀንዳ እንደሚሆንም ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማዘጋጀት በመመረጧ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ያሉ ሲሆን፤ ለጉባኤው ስኬታማነት ሕብረቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ሰላም እና ደኅንነት የአፍሪካ አንገብጋቢ አጀንዳ መሆኑን የገለጹት ሊቀ መንበሩ ሱዳን፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሊቢያን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ኢ-ሕገመንግሥታዊ ለውጦች አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው፤ ሀገራት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንዲያከብሩ አሳስበዋል። የአፍሪካ ሕብረት ተቋማዊ ሪፎርም እና ኢኮኖሚያዊ ትሥሥርን ጨምሮ ለአህጉራዊ አጀንዳዎች እየሠራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። አህጉራችን ፈተናዎች ቢኖሩባትም በጋራ ከቆምን እናልፋቸዋለን ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የዛሬው ስብስባ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን፤ የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ መሆኑ ይታወቃል።
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ይጀመራል
Jan 12, 2026 268
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚደረግ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣የሕብረቱ አባል አገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብስባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል አገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 589
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 534
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 747
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 894
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 565
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 513
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 1150
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3478
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3118
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1985
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7802
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6289
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት
Jan 14, 2026 205
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት ብርቱዎች ነገን በማሰብ ሁሌም ታትረው ይሰራሉ፤ ይደክማሉ፤ ይጥራሉ…ለቀጣዩ ትውልድም ጥሪት በማስቀመጥ አሻራቸውን ያኖራሉ። አገር የምትገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው። “አባት ያበጀው፤ ለልጅ ይበጀው” እንደሚባለው ልጆች ከአባቶቻቸው ያገኙትን ጥሪት በአዲስ እውቀትና አሰራር ለአገር እድገት በሚበጅ መልኩ አጠናክረው መጠቀማቸው አይቀርም። “ዕድሜ ጸጋ ነው” የሚለው አባባል አንዳንዴ በዕድሜ ብንገፋም ጠንክረን ከሰራን ብዙ ነገር እናያለን ከሚለው ጋር የተያያዘ ነው። በሰቆጣ ከተማም እድሜ ሳይገድባቸው በልማት ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ለዚህ ማሳያ ናቸው። የከተማዋ ነዋሪ የ67 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ አወቀ እና የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ዕድሜያቸው ቢገፋም ጠንክሮ ከተሰራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና ዕድሜ ጸጋ ሆኖ ብዙ ለውጥ ማየት እንደሚቻል ማሳያ ናቸው። ግለሰቦቹ ከዕድሜ ብዛት ጉልበቴ ደከመ፣ አይኔ ፈዘዘ፣ እጄም ተሳሰረ…ሳይሉ ጊዜያቸውን በደን፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ በማሳለፍ ለወጣቶች የልማት አርአያነት ያለው ተግባር እየፈጸሙ ነው። አቶ ብርሃኑ አወቀ በሰቆጣ ከተማ ዳርቻ የሚገኝ አለቱ ያገጠጠና የተራቆተ አካባቢን ከሌላ አካባቢ ለም አፈር በማምጣትና በመደልደል አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ደን በማልማት ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ነው። ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከወጣሁ ጀምሮ ጠንክሬ በመስራት የምለወጥበትን ሥራ ማሰብ ስነበረብኝ፤ የቆሻሻ መጣያ ሆኖ ለዘመናት የቆየን ጭንጫ መሬት ጠርጌና ደልድዬ ማልማት ችያለሁ ይላሉ ወደኋላ መልስ ብለው የተነሱበትን ሁኔታ ሲያስታውሱ። ግማሽ ሄክታር በማይሞላ መሬት ላይ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ዘይቱና፣ ጌሾ፣ ቡና፣ ማንጎና አቮካዶ አልምተዋል። በተጨማሪም ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመንና ሽንኩርት በማምረት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ጥሪት አፍርተዋል። ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ተግቶ መስራት ከተቻለ ሀብት ማፍራትና ህይወትንም መለወጥ እንደሚቻል የገለጹት አቶ ብርሀኑ፣ ወጣቱም ከእሳቸው የሥራ ትጋት በመማር በአካባቢው ያለውን ፀጋ ለይቶ በማልማት ሊጠቀም ይገባል ሲሉ ይመክራሉ። ሌላው የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ባለፉት 18 ዓመታት በተሰማሩበት የአትክልትና ደን ልማት ሥራ የአካባቢያቸውን ገጽታ ቀይረዋል። የዕድሜ ዘመናቸውን በውትድርናና በመንግስት ሠራተኝነት በማገልገል ሃገራዊ ግዳጃቸውን ሲወጡ ነው የቆዩት። ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከተገለሉ በኋላም ቤት ውስጥ መቀመጥን አልመረጡት። አካፋና ዶማቸውን ይዘው ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ ጌሾ፣ ዘይቱና እና ማንጎ በማልማት ምርቱን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። በአካባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ለይተን ማልማት ከቻልን ድህነትን ማስወገድ የሚከብድ አይሆንም ያሉት አቶ ታደሰ፣ የተራቆተና በጎርፍ የተጎዳን መሬት በማልማት አካባቢውን ሳቢና ማራኪ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት። ወጣቱም ከእሳቸው አርአያነት ያለው ተግባር በመማር በአካባቢው እጁ ላይ ባለ ሀብት ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል በተግባር ማሳየት እንዳለበት መክረዋል። የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ እንደገለጹት፤ በብሔረሰብ አስተዳደሩ 24ሺህ 847 አርሶ አደሮች በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተዋል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል ዕድሜ ሳይገድባቸው ወደ ልማት የገቡ አረጋዊያን እያከናወኑት ያለው የግብርና ልማት ሥራ ለወጣቱ ትልቅ ትምህርት እንደሚሆንም ተናግረዋል። ከእነሱ ልምድ በመውሰድ በዞኑ ወጣቶች፣ ሴቶችና አረጋዊያን በጓሮና ባላቸው መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲያለሙ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ይህም በዞኑ የሚስተዋለውን የስርዓተ ምግብ ችግር ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።
ከማላጋ እስከ አፍሪካ ዋንጫ፤ የሞሮኮው አዲስ እንቁ ብራሂም ዲያዝ
Jan 13, 2026 232
የግል ክህሎት፣ ፈጣን አስተሳሰቡ እና በጠባብ ክፍተቶች ውስጥ ሰብሮ የመግባት አቅሙ ሙገሳ እንዲጎርፍለት አድርጓል። አንድ ለአንድ ሲገናኝ ተከላካዮችን በፈጣን አካላዊ ቅልጥፍና እና በድንገት አቅጣጫ በመቀየር የሚያልፍበት መንገድ እንዲሁም የመፍጠር አቅሙ የተመልካቾችን ቀልብ የሚይዝ ነው። የአማካይ እና የአጥቂ መስመርን በማገናኘት እና በአስገራሚ ሁኔታ አጭር ኳሶችን በማቀበልም የተዋጣለት ተጫዋች ነው ማለት ይቻላል። በቦታ አያያዙ የእግር ኳስ ልኅቀቱ ከፍተኛ ነው የሚል አድናቆት ከእግር ኳስ ባለሙያዎች አግኝቷል። ኳስን ሲያንከባልልም ለዐይን ይስባል። ከክህሎቱ እና ከማራኪ እንቅስቃሴው ባለፈ ወደ ኋላ እየመለሰ ተከላካዮችን ያግዛል፣ ኳስ ይነጥቃል። ይህ ተጫዋች የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ክስተት የሆነው የሞሮኮው ብራሂም ዲያዝ ነው። የ26 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ዲያዝ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አምስት ጨዋታዎችን አድርጎ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ነው። አዘጋጇ ሞሮኮ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ መክፈቻ ኮሞሮስን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የውድድሩን የመጀመሪያ ግብ አስቆጥሯል። ብራሂም አብዱልቃድር ዲያዝ የተወለደው እ.አ.አ ኦገስት 3 ቀን 1999 በስፔን ማላጋ ግዛት ነው። እናቱ ስፔናዊ አባቱ ሞሮኳዊ ናቸው። ዲያዝ ያደገው በማላጋ ነው። እግር ኳስንም በአንዳሉሺያዊቷ ከተማ ሲጫወት ቆይቷል። በ16 ዓመቱ ካደገበት ማላጋ በመውጣት እ.አ.አ በ2015 ወደ ማንችስተር ሲቲ ወጣት አካዳሚ በ200 ሺህ ፓውንድ ወጪ ተዘዋወረ። ዲያዝ እ.አ.አ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2016 በካራባኦ ካፕ (በቀድሞ አጠራሩ ሊግ ካፕ) ማንችስተር ሲቲ ከስዋንሲ ሲቲ ባደረገው ጨዋታ በ80ኛው ደቂቃ በኬሌቺ ኢናቺዩ ተቀይሮ በመግባት ለውኃ ሰማያዊዎቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያውን ጨዋታ ካደረገ ከሶስት ቀናት በኋላ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለሶስት ዓመታት የሚያቆየውን ፕሮፌሽናል ኮንትራት ተፈራርሟል። እ.አ.አ ኖቬምበር 21 ቀን 2017 ማንችስተር ሲቲ ከፌይኖርድ ሮተርዳም ጋር ባደረገው የሻምፒዮናስ ሊግ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል። በወቅቱ ብራሂም ስተርሊን መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ሰዓት ላይ ነበር ተቀይሮ የገባው። ዲያዝ በውኃ ሰማያዊዎቹ ማልያ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የተጫወተው እ.አ.አ ዲሴምበር 19 ቀን 2017 ነው። ማንችስተር ሲቲ ከሌስተር ሲቲ በካራባኦ ካፕ ጨዋታ ላይ ለ88 ደቂቃዎች ተሰልፎ ተጫውቷል። እ.አ.አ ጃንዋሪ 20 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን 3 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በወቅቱ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ያነሳ ሲሆን፤ በውድድር ዓመቱ አራት ጨዋታዎች ላይ ብቻ ተሳትፎ ያደረገው ብራሂም ዲይዝ የሜዳሊያ ሽልማት አግኝቷል። እ.አ.አ ኦገስት 5 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ቼልሲን 2 ለ 0 ባሸነፈበት የኮሙዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ላይ በፊል ፎደን ተቀይሮ በመግባት ለ15 ደቂቃዎች ተጫውቷል። ዲያዝ እ.አ.አ 2018/19 ማብቂያ ላይ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የመጀመሪያ ግቦቹን ለሲቲ አስቆጥሯል። በማንችስተር ሲቲ ያለው ውል እ.አ.አ 2019 ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት ስሙ ከዝውውር ጋር በስፋት ይነሳ ነበር። ዲያዝ እ.አ.አ ጥር 2019 በ17 ሚሊዮን ዩሮ ከማንችስተር ሲቲ ወደ ሪያል ማድሪድ ተዘዋወረ። ለስድስት ዓመታት የሚያቆየውን ውልም ፈርሟል። የክንፍ ተጫዋቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን በነጮቹ ማልያ ያደረገው እ.አ.አ ጥር 9 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ ሌጋኔን በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ 3 ለ 0 ባሸነፈበት ወቅት ነው። ከአራት ቀናት በኋላ በስፔን ላሊጋ ሪያል ማድሪድ ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ ተቀይሮ በመግባት በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያ ግቡን ለማስቆጠር ሶስት ወራትን ጠብቋል። እ.አ.አ ግንቦት 12 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ በላሊጋው በሪያል ሶሲዬዳድ 3 ለ 1 ሲሸነፍ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በወቅቱ ዲያዝ ስድስት ጨዋታዎች ላይ በላሊጋው የተጫወተ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ዓመቱ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ሪያል ማድሪድ እ.አ.አ በ2021/21 የውድድር ዓመት ብራሂም ዲያዝ ወደ ኤሲ ሚላን በውሰት ማምራቱን ይፋ አደረገ። ዲያዝ ሚላን እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2020 ክሮቶኔን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ የመጀመሪያ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ ግንቦት 2021 ኤሲ ሚላን ጁቬንቱስን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ያስቆጠረው ግብም ተጠቃሽ ነው። ዲያዝ በኤሲ ሚላን የውሰት ውሉ ሲያበቃ በድጋሚ ለሁለት ዓመታት በውሰት የሚቆይበት ስምምነት ሪያል ማድሪድ ከጣልያኑ ክለብ ጋር የተፈራረመ ሲሆን፤ ውሉ ሚላን ተጫዋቹን የማቆየት መብት ሰጥቶታል። እ.አ.አ መስከረም 15 ቀን 2021 ኤሲ ሚላን በሻምፒዮንስ ሊጉ የ3 ለ 2 ሽንፈት ሲያስተናግድ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ግቡን አስቆጥሯል። በ2023 ኤሲ ሚላን ቶተንሃም ሆትስፐርስን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ 1 ለ 0 ሲያሽንፍ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023 ሰኔ ወር ላይ ሪያል ማድሪድ ዲያዝ ከኤሲ ሚላን የሶስት ዓመታት የውሰት ቆይታ በኋላ ወደ ክለቡ መመለሱን አሳውቋል። ተጫዋቹ በኤሲ ሚላን ቆይታው 91 ጨዋታዎችን አድርጎ 13 ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ዲያዝ ወደ ሪያል ማድሪድ ከተመለሰ በኋላ ኮንትራቱን እስከ 2027 አራዝሟል። እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2023 ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ሪያል ማድሪድ ላስ ፓልማስን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። የክንፍ መስመር ተጫዋቹ ሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥ እና በአውሮፓ መድረክ በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ላይ ግብ በማስቆጠር እና ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ዲያዝ እስከ አሁን ለሪያል ማድሪድ ባደረጋቸው 129 ጨዋታዎች 20 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከነዚህም ውስጥ 13ቱ በላሊጋው ያስቆጠራቸው ናቸው። ከክለብ ወጣ ስንል የተጫዋቹን የብሔራዊ ቡድን ቆይታ እናገኛለን። ዲያዝ በታዳጊነቱ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ለስፔን ወጣት ቡድኖች ተጫውቷል። እ.አ.አ በ2016/17 የውድድር ዘመን ለስፔን ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በ16 ዓመቱ ተሰልፎ መጫወት ችሏል። በተለይም አዘርባጃን እ.አ.አ በ2017 ባዘጋጀችው 15ኛው የአውሮፓ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ላይ ያሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆት አስችሮታል። በዚያ ቀጥለው በነበሩ ዓመታትም ለስፔን ከ19 እና ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቷል። ብራሂም ዲያዝ በስፔን ታዳጊና ወጣት ቡድኖች ላይ በአጠቃላይ 28 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። የስፔን ታዋቂ የስፖርት ጋዜጣ ማርካ እ.አ.አ ጥር 23 ቀን 2023 ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን መጫወት ማቀዱን የሚመለከት ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ከዜግነቱ ጋር በተያያዘ ያሉ አንዳንድ የአስተደዳር ጉዳዮች በወቅቱ መፍትሄ አግኝተዋል። ይሁንና ኮትዲቯር እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሞሮኮው አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከተጫዋቹ ጋር በተደረገ የቅድሚያ ስምምነት ለተጫዋቹ ጥሪ አልተደረገለትም። ዲያዝ እ.አ.አ መጋቢት 10 ቀን 2024 ለሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሀገሪቷ ብሔራዊ መጫወት እንደሚፈልግ በይፋ ማሳወቁን ማርካ በወቅቱ ዘግቧል። ጥያቄውም ተቀባይነት አገኘ። በወቅቱ የሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ብሔራዊ ቡድኑ ከአንጎላ እና ሞሪታኒያ ጋር ለነበረበት የወዳጅነት ጨዋታ ለዲያዝ ጥሪ አድርገውለታል። እ.አ.አ መጋቢት 22 ቀን 2024 ሞሮኮ አንጎላን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። እ.አ.አ ጥቅምት 6 ቀን 2024 ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከጋቦን ጋር ባደረገችው ጨዋታ 4 ለ 1 ስታሸንፍ የመጀመሪያ ግቡን ለሞሮኮ ማስቆጠር ቻለ። እ.አ.አ ሕዳር 15 ቀን 2024 ሞሮኮ በማጣሪያው ጋቦንን 5 ለ 1 ስትረታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። ከሶስት ቀናት በኋላ ሞሮኮ ከሌሴቶ ጋር ባደረገችው የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ 7 ለ 0 ስታሸንፍ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር በሀገሩ ማልያ የመጀመሪያ ሀትሪኩን ሰርቷል። እ.አ.አ ጥቅምት 2025 ሞሮኮ ራባት ላይ ኮንጎ ሪፐብሊክን 1 ለ 0 በማሸነፍ በስፔን ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተይዞ የነበረውን 15 ተከታታይ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ክብረ ወሰን በመስበር ወደ 16 ማድረስ ችላለች። በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ ላይ ዲያዝ ተሰልፎ ተጫውቷል። የሞሮኮ ተከታታይ የማሸነፍ ጉዞ 19 ጨዋታዎች ደርሶ የነበረ ሲሆን በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከማሊ ጋር አንድ አቻ ስትለያይ አብቅቷል። ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማጣሪያ ብታልፍም አስቀድማ ውድድሩን እንድታዘጋጅ እድል አግኝታ የነበረው ጊኒ በዝግጅት ማነስ ምክንያት በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ከሁለት ዓመት በፊት አዘጋጅነቷ ተነጥቆ ለሞሮኮ ተሰጥቷል። ሞሮኮ የዘንድሮውን ውድድር በደማቅ ሁኔታ እያካሄደች ትገኛለች። በውድድሩ ላይ ጎልተው ከታዩ ተጫዋቾች መካከል ብራሂም ዲያዝ ተጠቃሽ ነው። በአፍሪካ ዋንጫው እስከ አሁን ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። በተሰለፈባቸው በእያንዳዱ ጨዋታዎች ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን በአምስት የአፍሪካ ዋንጫ ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። ሞሮኮ በሩብ ፍጻሜው ማሊን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሯል። ሀገሩ ወደ ግማሽ ፍጻሜ እንድታልፍ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱንም እየመራ ይገኛል። ሞሮኮ በዚሁ ግስጋሴዋ ከቀጠለች ዲያዝ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና ኮከብ ተጫዋች የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። ሞሮኮ በግማሽ ፍጻሜው ከናይጄሪያ ጋር ረቡዕ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ታደርጋለች። ዲያዝ በዚህ ጨዋታ ላይ ልዩነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። አንዳንድ የእግር ኳስ ተንታኞች ብራሂም ዲያዝ እ.አ.አ በ2026 ወጥነት ያለው ብቃት ማሳየት ከቻለ የአፍሪካ ኮከብ ተጫዋችነት ሽልማቱን የሚወስድበት የለም እያሉ ይገኛሉ። ሞሮኳውያን በተጫዋቹ ፍቅር ልባቸው ከንፏል። በየጨዋታው ዲያዝ ዲያዝ እያሉ ከፍተኛ ድጋፍ እና ሙገሳ እየሰጡት ይገኛሉ። እሱም በድንቅ ብቃቱ ምላሽ እየሰጣቸው ነው። በተወለደበት ማላጋ ከተማ የጀመረው የእግር ኳስ ሕይወት በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የበለጠ አብቧል። የሞሮኮው አዲሱ ኮከብ ብራሂም ዲያዝ ቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወት በስኬት እና በድል የደመቀ እንደሚሆን ከአሁኑ ድንቅ ብቃቱ ተነስቶ መናገር ይቻላል።