ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ሲዳማ ቡና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ተረከበ
Jul 5, 2026 144
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦ በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ሀብታሙ በ70ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ጎሉን አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ54 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና በ68 ነጥብ ዓመቱን ጨርሷል። ጨዋታውን ተከትሎ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉ አሸናፊ የሆነው ሲዳማ ቡና ዋንጫውን ተረክቧል። የሊጉ ዋንጫ ሲዳማ ቡና በ1999 ዓ.ም ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ያሳካው ትልቁ ድሉ ነው። ሻምፒዮንነቱን ተከትሎ በቀጣዩ ዓመት ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣዩ ዓመት በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ይሳተፋል። ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ዋንጫውን ለማንሳት ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ይፋለማል። በዋንጫ ስነ ስርዓቱ ላይ በርካታ የሲዳማ ቡና ደጋፊዎች ታድመዋል። በተጨማሪም ሲዳማ ቡና ዛሬ የተጠናቀቀውን ከ20 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በማጠቃለያ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻን በመለያ ምት በመርታት ዋንጫውን አንስቷል። በዚህም ድርብ ድል አሳክቷል። በሊጉ የመዝጊያ ስነ ስርዓት የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የፕሪሚየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው የዘንድሮው የሊጉ ውድድር ዛሬ በ38ኛ ሳምንት ተቋጭቷል። ምድረ ገነት ሽሬ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ መቀሌ 70 እንደርታና አርባምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረዱ ክለቦች ናቸው። ከከፍተኛ ሊግ ያደጉት ሃላባ ከተማ እና ጋሞ ጨንቻ በቀጣዩ የውድድር ዓመት በሊጉ ይሳተፋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ ናትናኤል ዳንኤል እና የፋሲል ከነማው ታምራት እያሱ በተመሳሳይ 15 ጎሎች በጋራ የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን አጠናቀዋል። የሲዳማ ቡናው አቤል ያለው በ14 ግቦች ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል።
በአማራ ክልል የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው
Jul 5, 2026 210
ጎንደር ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ባለፉት ዓመታት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን የአማራ ክልል ሴቶች፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ በጎንደር ከተማ አካሄዷል። የቢሮ ኃላፊዋ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው። ለአብነትም በበጀት ዓመቱ በባህር ዳርና ደብረ ማርቆስ ከተሞች ከ266 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። የገበያ ማዕከላቱም ተደራጅተውና በግል የሙያ ዘርፎች የስራ ዕድል ለሚፈጠርላቸው ሴቶች የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ችግርን ለመቅረፍ የሚያስችሉ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የማዕከላቱ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅም ለ100 ሴቶች ቋሚ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ እንዲያገኙ ዕድልን እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል። በገቢ ማስገኛ ፕሮግራሞች፣ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ የሴቶችንና የህጻናትን መብት በማስጠበቅና በሌሎች ተያያዥ ተግባራት የተጀመሩ ስራዎች በአዲሱ በጀት ዓመት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሴቶች፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ቀኑ ቢያድጎ በበኩላቸው፣ በበጀት ዓመቱ ለ33 ሺህ ሴቶች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረ ገልጸዋል። በተጨማሪም ሰባት የህፃናት ማቆያዎችን በማስገንባት የሚያጠቡ እናቶች ልጆቻቸውን በቅርበት እየተከታተሉ መደበኛ ስራቸውን በትጋት እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎትም አቅመ ደካሞችን፣ ህጻናትን፣ የአካል ጉዳተኞችንና ሌሎች ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመደገፍ ስራ መሰራቱን አስረድተዋል። "ያለዕድሜ ጋብቻን ጨምሮ ከሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች ነጻ የሆኑ 25 ቀበሌዎች ተፈጥረዋል" ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ አስተዳደር የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉቀን ጌታሁን ናቸው። በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ በተለያየ ምክንያት ለተቸገሩ 64 ሴቶች ከክልሉ በተገኘ 6 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ድጋፍ የማቋቋም ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በዕለቱም በጎንደር ከተማ የተገነባውን የሴቶችና ህጻናት የተሃድሶ ማዕከል ወደ ስራ የማስገባት ተግባር ተከናውኗል።
የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል ተችሏል- አቶ ሽመልስ አብዲሳ
Jul 5, 2026 400
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በበጀት ዓመቱ የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል መቻሉን የፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ። አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዳሉት በ2018 በጀት ዓመት በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማትንና የዜጎችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል። የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ክፍፍል ሥርዓት በጥናትና በተደራጀ ዕቅድ እንዲመራ ከማድረግ ባሻገር ወደ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚተላለፉ ሀብቶች ግልጽና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲከፋፈሉ ክትትልና ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል መቻሉን ገልጸዋል። ይህም የሚተላለፉ ሀብቶች ላይ ግልጽነትን ለማሳደግና የበይነ መንግሥታት የፊስካል ሽግግር ሥርዓትን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አብራርተዋል። በተጨማሪም የፌዴራል መሠረተ ልማት ስርጭት ፍትሐዊነትን ማስፈን እንዲሁም ልዩ ዓላማ ያላቸው ድጎማዎች በግልጽነትና በተጠያቂነት መርህ ለክልሎች መከፋፈላቸውን ማረጋገጥ የኮሚቴው ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ተግባራት እንደነበሩ አመልክተዋል። የኢኮኖሚና የማሕበራዊ ዕድገትን ማፋጠንና በክልሎች መካከል ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ የረጅም ጊዜ ጥረት እንደሚጠይቅ ገልጸው ማነቆዎችን በመለየትና መረጃዎችን በወቅቱ በማሰባሰብ ዘላቂ መፍትሔዎችን ለማምጣት ይሰራል ማለታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት መረጃ ያመለክታል።
ተመራቂ እጩ መምህራን በስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ሙያዊ ሃላፊነት አለባቸው
Jul 5, 2026 221
ሰቆጣ ፤ሰኔ 28/2018(ኢዜአ)፡- ተመራቂ እጩ መምህራን በስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ሙያዊ ሃላፊነታቸውን መወጣት አለባቸው ሲሉ የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ ገለፁ። የሰቆጣ መምህራን ኮሌጅ በዲግሪና በዲፕሎማ ደረጃ ያስተማራቸውን 484 እጩ መምህራንን በዛሬው እለት አስመርቋል። በምረቃው ላይ የተገኙት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ በወቅቱ፤ ሀገራችን ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ የትምህርት ዘርፉ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ብለዋል። ተተኪው ትውልድ የተማረና በፈጠራ ክህሎት የዳበረ እውቀት እንዲገነባ ለማስቻል መምህራን ያላቸው ድርሻም የላቀ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ተመራቂ እጩ መምህራን ሀገር አሻጋሪና በስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ሙያዊ ሃላፊነት አለባችሁ ብለዋል። የሰቆጣ መምህራን ኮሌጅ ዲን ወርቁ ጌጡ እንዳሉት ኬሌጁ ዕጩ መምህራንን በመደበኛና በክረምት መርሃ ግብሮች በማስተማር ለትምህርት ስርዓቱ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል። በዘንድሮው ዓመትም በዲግሪና በዲፕሎማ ደረጃ ያስተማራቸውን 484 እጩ መምህራንን በዛሬው እለት ማስመረቁን አስረድተዋል። በዛሬው እለት ካስመረቃቸው መካከል ኮሌጁ ለመጀመሪያ ጊዜ በኽምጣኟ ቋንቋ በዲግሪ መርሃግብር ያስተማራቸው ዕጩ መምህራን ይገኙበታል ብለዋል። ዕጩ መምህራን የተማረ ዜጋ ለመቅረፅና በፈጠራ የበለፀገ ትውልድ እንዲፈጠር የሙያ ግዴታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በዲግሪ መርሃ ግብር ተመራቂ ዕጩ መምህር ወርቄ ደሳለኝ እንዳሉት በኮሌጁ ባገኙት እውቀት በራስ የሚተማመን የተማረ ዜጋ ለመፍጠር ሙያዊ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ዕጩ መምህር ኪሮስ ተክሌ በበኩላቸው በተማሩት የመምህርነት ሙያ በፈጠራ የበለፀገና የተማረ ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ርብርብ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።
የሐረሪ ባህልና ስፖርት ፌስቲቫል በአሜሪካዋ ሜምፊስ ከተማ እውቅና አገኘ
Jul 5, 2026 229
አዲስ አበባ፤ሰኔ 28/ 2018(ኢዜአ):-በአሜሪካዋ ሜምፊስ ከተማ የሐረሪ ባህልና ስፖርት ፌስቲቫል የከተማዋ በዓል ሆኖ እንዲከበር የከተማው ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ ወስኗል። በከተማው የሀረሪ ማህበረሰብ በየአመቱ የሚያከብሩት የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል አከባበር እውቅና ማግኘቱ ባህሎቻቸውን፣ታሪኮቻቸውንና እሴቶቻቸውን ለሌላው ማህበረሰብ በላቀ ደረጃ ለማስተዋወቅ እንደሚያስችል ተጠቅሷል። እውቅናው ከዚህ በተጨማሪም በተለያዩ አለማት ለሚገኙ የሐረሪ ማህበረሰብ ትልቅ ኩራት ከመሆኑ ባሻገር የጥንታዊ ባህሎቻቸውን ጠብቆ ለማቆየትና ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ትልቅ መነሳሳትን የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል። የከተማዋ ምክር ቤት የሰጠው እውቅናም ከተማዋ ለባህል ብዝሃነት፣ለህዝቦች የእርስ በእርስ ትውውቅና ትስስር እንዲጠናከር ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ተመላክቷል። እንዲሁም በሜምፊስና በሐረር ከተሞች መካከል የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ተጠቁሟል። በዓሉም በየአመቱ July 1 ቀን እንዲከበር ምክር ቤት በአዋጅ ደንጓል።
ፖለቲካ
ባገኘነው ዕውቀት ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በመጠቀም ሀገራችንን ለማገልገል ተዘጋጅተናል
Jul 5, 2026 390
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 28 /2018(ኢዜአ) ፦ያገኘነው ዕውቀት ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በተሻለ መንገድ እንድንረዳው አድርጎናል፤ ይህን ተጠቅመን ሀገራችንን ለማገልገል ተዘጋጅተናል ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ተመራቂዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተመራቂዎች አስመርቋል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመራቂዎች እንደገለጹት፤ በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ የተሰጣቸው ሥልጠና ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። ከተመራቂዎቹ መካከል የኢፌዴሪ አየር ኃይል የ3ኛ አየር ምደብ ምክትል አዛዥ እና የተዋጊ ሄሊኮፕተር አብራሪና አስተማሪ ኮሎኔል ደረስ እንዳለ እንደገለጹት፤ በኮሌጁ ያካበቱት እውቀት ሀገሪቱ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን በግልጽ ለመረዳትና ለመተንተን የሚያስችል ከፍተኛ አቅም ፈጥሮላቸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ የምትገኝበት የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን ተለዋዋጭ ሁኔታ በውል ለመረዳት ማስቻሉን ገልጸው፤ ይህንን ስትራቴጂካዊ ዕይታ መሠረት በማድረግ ሀገራቸው የምትሰንቀውን ታላቅ ህልምና ግብ ለማሳካት በቁርጠኝነት ለመስራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል። ሌላው አስተያየታቸውን የሰጡት ከመከላከያ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ሌተናል ኮሎኔል ዶክተር ቴዎድሮስ ገብረ ሩፋኤል በበኩላቸው፤ በስትራቴጂክና ደኅንነት ጉዳዮች ላይ የተከታተሉት ትምህርት ዘርፈ-ብዙ ሁኔታዎችን በጥልቀት ለመተንተን ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን ጠቁመዋል። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የበዙበት መሆኑን አመልክተው፤ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በትብብር መንፈስ የሚንቀሳቀሱ ከሆነ የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ በጎ ውጤት እንደሚያስገኙ አመልክተዋል። ሌላው ሰልጣኝ ከአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ የመጡት አቶ ጌታሰው ደሴ እንዳሉት፤ ሥልጠናው ለሀገር አንድነት፣ ለሀገር ፋይዳ እና ለተቋማት ግንባታ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ አስተዋጽኦ ለማበርከት ትልቅ አቅምና ወደፊት ለሚሰማሩበት የሥራ መስክም ስንቅ እንደሆናቸው ገልጸዋል። በተመሳሳይ ከልዩ ዘመቻዎች እዝ የመጡት ሌተናል ኮሎኔል ደረጀ ዳባሳ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ያገኙት ዕውቀት የእለት ተእለት ተግባራቸውና ከሙያቸው ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ ስትራቴጂካዊ አካባቢውን፣ ጂኦፖለቲካውን እና አጠቃላይ ሁኔታውን በተገቢው መንገድ ለመረዳት አስችሏቸዋል። ትምህርቱ ለተግባራዊ ስራቸው ጠንካራ መነሻ ከመሆኑም በላይ፣ ባላቸው የረጅም ጊዜ ልምድ ላይ ትልቅ አቅም የገነባ መሆኑንም አክለዋል። የኮሌጁ ሰልጣኝ የሆኑት ኮሎኔል እማምር አያሌው በበኩላቸው፤ ቀጣናዊና የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ በደንብ በመረዳት መተንተን የሚችል ጠንካራ ሰራዊት እየተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም በአስተሳሰብ የበሰለ፣ በስትራቴጂካዊ እውቀት የዳበረና ለማንኛውም ሀገራዊ ግዳጅ ዝግጁ የሆነ ሠራዊት መገንባቱን ጠቁመዋል፡፡
ህዝቡ አሉታዊ የሆኑ የውስጥ እና የውጭ ተጽዕኖዎች ሳይበግሩት በምርጫው ያሳየው ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ የሚደነቅ ነው-የጋራ ምክር ቤቱ
Jul 5, 2026 468
አዲስ አበባ፤ሰኔ 28/ 2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ህዝብ አሉታዊ የሆኑ የውስጥ እና የውጭ ተጽዕኖዎች ሳይበግሩት በምርጫው ያሳየው ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ ገለፁ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደትን አስመልክቶ ውይይት አድርጓል። ምክር ቤቱ በጉባኤው ከተወያየባቸው ጉዳዮች መካከል የፖለቲካ ፓርቲዎች ከ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ስለሚወስዱት ትምህርትና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ይገኙበታል። እንዲሁም የሂደቱ ተዓማኒነት እና አካታችነትን በተመለከተ በቀጣይ ምን መደረግ እንዳለበት እና በጋራ መፍትሄዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። የጉባኤው ተሳታፊዎችም ህዝቡ አሉታዊ የሆኑ የውስጥ እና የውጭ ተጽእኖዎች ሳይበግሩት ያሳየው ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን አቶ ሰለሞን አየለ ለኢዜአ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁ በውይይቱ ላይ ተገልጿል። ለዚህም ስኬት የበኩላቸውን ሃላፊነት ለተወጡ የፀጥታና የደህንነት አካላት፤ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ፣ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የጋራ ምክር ቤቶች አመራሮች እና ሌሎች አካላት የጋራ ምክር ቤቱ ምስጋና ያቀርባል ብለዋል።
ለውይይት የቀረቡት አጀንዳዎች ዘመናትን ለተሻገሩ አለመግባባቶች ዘላቂ መፍትሔን በመስጠት የኢትዮጵያን መጻኢ ጉዞ የሚወስኑ ናቸው
Jul 5, 2026 366
ሀዋሳ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለምክክር ጉባኤው ያዘጋጃቸው ስምንቱ አጀንዳዎች፣ ዘመናትን ለተሻገሩ አለመግባባቶች ዘላቂ መፍትሔን በመስጠት የኢትዮጵያን መጻኢ ጉዞ የሚወስኑ መሆናቸውን የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ገለጸ። ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት አሳታፊ በሆነ መንገድ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሰበሰባቸውን አጀንዳዎች መነሻ በማድረግ፣ ከሐምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሄደው ዋና የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንት አጀንዳዎችን ለይቶ አቅርቧል፡፡ በጉባኤው አጀንዳዎች ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረገው የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወጣት በቃሉ መሰረት፤ ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት አሳታፊ በሆነ መልኩ አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ሥራ ማከናወኑን ገልጿል። ሂደቱ በርካታ ምዕራፎችን አልፎ ለዚህ መብቃቱን ያደነቀው ወጣት በቃሉ፣ ለዋናው የምክክር ጉባኤ የተለዩት አጀንዳዎች ዘመናትን ለተሻገሩ አለመግባባቶች ዘላቂ መፍትሔ በመስጠት የኢትዮጵያን መጻኢ ጉዞ የሚወስኑ መሆናቸውን ጠቁሟል። በአጀንዳዎቹ ላይ በጥልቀት በመወያየት ለችግሮቹ ዘላቂ መፍትሔን መሻት እንደሚገባ ጠቅሶ፣ ይህንን ወርቃማ ዕድል ማባከን እንደማይገባና ሂደቱ ፍሬያማ እንዲሆን ሁሉም ዜጋ የሚጠበቅበትን እንዲወጣም አሳስቧል፡፡ የማህበሩ አባል የሆነችው ወጣት በረከት ጴጥሮስ በበኩሏ፤ የሀገርን ልማትና ሰላም ለማስቀጠል ልዩነቶችን በውይይትና በንግግር መፍታት ወቅቱ የሚጠይቀው የሰለጠነ መንገድ መሆኑን ተናግራለች፡፡ ኮሚሽኑ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ልዩነት የፈጠሩና የግጭት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት የጋራ መግባባትን ለመፍጠር ያዘጋጃቸው አጀንዳዎች ዘላቂ ሰላምን የሚያመጡና ጠንካራ ሀገርን የሚፈጥሩ መሆናቸውን ገልጻለች፡፡ እንደ ሀገር የተፈጠሩ ልዩነቶችንና ለግጭት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በምክክር ለመፍታት የሚደረገው ጥረት ለኢትዮጵያውያን ትልቅ ዕድል መሆኑን የገለጸው ደግሞ የክልሉ ወጣቶች ማህበር ሥራ አስፈጻሚ ወጣት አሸናፊ ኤፍሬም ነው፡፡ ኮሚሽኑ ለምክክር ጉባኤው የለያቸው አጀንዳዎች ለበርካታ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡና የበለጸገች ሀገርን ለትውልድ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ተናግሯል፡፡ ኮሚሽኑ ከዋናው ጉባኤ በፊት በየደረጃው ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ሲያደርግ የነበረው ውይይት በጠረጴዛ ዙሪያ የመነጋገር ባህልን ማሳደጉን የጠቀሰው ወጣት አሸናፊ፣ ምክክሩ የታለመለትን ውጤት እንዲያመጣ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባም ጥሪውን አስተላልፏል።
የሰላም ጥሪ በመቀበል ከጥፋታችን ተምረን ለልማትና ሰላም ግንባታ አርአያ በመሆን እየሰራን ነው-የቀድሞ ታጣቂዎች
Jul 5, 2026 422
ደብረ ብርሃን፤ሰኔ 28/ 2018(ኢዜአ)፡- የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ከጥፋታችን ተምረን ለልማትና ለሰላም ግንባታ አርአያ በመሆን እየሰራን ነው ሲሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ገለጹ። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ህብረተሰቡን ተቀላቅለው በልማት ስራ ላይ የተሰማሩ የቀድሞ ታጣቂዎችን የኢዜአ ሪፖርተር አነጋግሯቸዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል አጎላላና ጠራ ወረዳ የሚኖረው አወቀ ስለሺ፤ በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት ማህበረሰቡንም ይሁን ቤተሰቡን የጎዱበት አጋጣሚ ሲያስታውስ ከፍተኛ ጸጸት የሚሰማው መሆኑን ገልጿል። በጫካ እንዲሰባሰቡ ያደረጓቸው አካላት ለዘረፋና ሃብት ማካበት የተሰለፉ መሆኑን በመረዳቱ የመንግስትን የሰላም ጥሪ መቀበሉን ተናግሯል። ከስልጠና በኋላ በተደረገለት የገንዘብ ድጋፍና በተሰጠው የመስሪያ ቦታ ወደ ልማት በመግባት ከራሱም አልፎ ቤተሰቡንና ማህበረሰቡን የሚጠቅም ተግባር ላይ መሰማራቱን ገልጿል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ከጥፋታችን ተምረን ለልማትና ለሰላም ግንባታ አርአያ በመሆን እየሰራን እንገኛለን፤ ይህንንም አጠናክረን እንቀጥላለን ሲል ተናግሯል። በመሆኑም በጫካ የሚገኙ ወጣቶች ይህንን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከጥፋት በመውጣት የልማትና የሰላም አርአያ ለመሆን እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። ሌላኛው የቀድሞ ታጣቂ ሚኪያስ ቸርነት፤ በተሳሳተ መልኩ ወደ ጫካ በመግባት በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ በፈፀመው በደል መፀፀቱን ገልጿል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል በተደረገለት ድጋፍ ወደ ልማት በመግባት ሰላማዊ ህይወት በመምራት ላይ መሆኑን ተናግሯል። በጠመንጃ ትግል ከጥፋት በስተቀር የሚመጣ አንዳችም ውጤት የሌለ መሆኑን በመረዳት ሰላምና ልማትን በመምረጥ እየሰራ መሆኑን ገልፆ፤ ሌሎች በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎችም ከተሳሳተ መንገዳቸው እንዲመለሱ አስገንዝቧል። በሰሜን ሸዋ ዞን የአጎለላና ጠራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አዳፍሬ ማንደፍሮ፤ የመንግስት የሰላም ጥሪ ብዙዎቹን ወደ ሰላማዊ ህይወት እየመለሳቸውና ሰርተውም እየተለወጡ መሆኑን ገልጸዋል። በጫካ የሚገኙ ሌሎች ታጣቂዎችም እየሄዱበት ያለው መንገድ የተሳሳተ እና ማህበረሰብን የሚጎዳ መሆኑን በመገንዘብ ጊዜ ሳያባክኑ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እንዲመጡ መልእክት አስተላልፈዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ምክትል ሃላፊ ዓባይ ዲሌ፤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን የመቀበልና በዘላቂነት የማቋቋም ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ በፊት የተመለሱት በተለያዩ የልማት መስኮች ተሰማርተው እየሰሩ ስኬታማ መሆናቸውን አንስተው፥ ሌሎች በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎችም የእነርሱን ፈለግ በመከተል እንዲመጡ ጥሪ አቅርበዋል። የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው የሚመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችን ለመደገፍና በዘላቂነት ለማቋቋም መንግስት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። በሰሜን ሸዋ ዞንና አካባቢው ያለውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት በተለይም የሃገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና አጠቃላይ ማህበረሰቡ የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
መከላከያ ሠራዊት የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት እየጠበቀ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Jul 4, 2026 1894
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት በአስተማማኝነት እየጠበቀ መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተመራቂዎች አስመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላምና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር)፣ የኮሌጁ አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ጥላሁን ደምሴ እና ከፍተኛ ጄኔራል መኮንኖች ተገኝተዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሥነ-ስርዓቱ ባስተላለፉት፤ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ የደህንነት ሁኔታ ውስብስብና ኢ-ተገማችነትን ታሳቢ ያደረገ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ቀጣናዊ የትብብር መርህ ለማደናቀፍ የታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች የሴራ ጥምረት ወይም "ፅምዶ" ፈጥረው እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊ ሰላምና ደህንነት በመጠበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለዘመናት በሰላም እጦት የሚገለፀው የቀይ ባሕርና አፍሪካ ቀንድ አከባቢ የደህንነት ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ እየተወሳሰበ መምጣቱን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው የምትገኝ፣ ከማንኛውም የቀጣናው ችግርና ተጠቃሚነት ማምለጥ የማትችል ትልቅ ሀገር መሆኗንም አስገንዝበዋል። ታሪካዊ ጠላቶችም ኢትዮጵያ ቀጣናውን የማረጋጋት የመሪነት ሚና እንዳትወጣና በውስጥ ጉዳዮች ብቻ እንድትጠመድ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በሌላ በኩልም ጎረቤቶችን እንዲታመሱ በማድረግ ለውስጣዊ ደህንነታችን ጫና መፍጠር የሚችሉ ሴራዎችን በመሸረብ ቀጣናውን ለማተራመስ አበክረው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ከባሕር ዳርቻ ለማስወጣት የተጠቀሙበት የረጅም ዘመናት ሴራም ዛሬ ላይ ፅምዶ በሚል ስያሜ ዕድሳት ተደርጐለት እየተስተጋባ ነው ብለዋል። የዘመኑ ጦርነት በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በረጅም ርቀት ሚሳኤሎች፣ በሰው አልባ መሣሪያዎችና በሳይበር ኦፕሬሽኖች የታገዘ የቴክኖሎጂ ጦርነት መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም አደረጃጀቱንና ዘመናዊ ትጥቁን በማጠናከር በማንኛውም አስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ቁመና ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ተመራቂዎችም የቀሰሙትን ስትራቴጂክ ዕውቀት ለሠራዊቱ ተጨማሪ ግንባታ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አሳስበዋል። የኮሌጁ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ጥላሁን ደምሴ በበኩላቸው፤ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት የተመሰረተው ኮሌጁ በተለዋዋጭ ስትራቴጂክ ምህዳር ውስጥ የብሔራዊ ኃይል ማስፈፀሚያ አቅሞችን ውጤታማ ለማድረግ እየሰራ ነው ብለዋል። ኮሌጁ የስርዓተ ትምህርት ማሻሻያ በማድረግ በጥናት፣ ምርምርና የደህንነት ትንተና ላይ ትኩረት አድርጎ የአመራር አቅም ግንባታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል። መንግሥት የኮሌጁን የመሰረተ ልማትና የዲጂታላይዜሽን አቅም በማሳደግ ወደ ስማርት ኮሌጅ ለመቀየር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የአስተዳደሩ ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላትን ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት ተገኝቷል
Jul 3, 2026 2092
ድሬደዋ፤ ሰኔ 26/2018(ኢዜአ)፦) የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የአስፈጻሚውን አካላት ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት መገኘቱን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አፈጉባኤ አብዲ ሙክታር ገለጹ። ምክር ቤቱ የስራ ዘመኑን መደበኛ ጉባኤ የፊታችን ሰኞ ያካሂዳል። የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር፣ ምክር ቤቱ የአስፈፃሚውን አካላት የአምስት አመታት የስራ እቅድና አፈጻጸም የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን አስመልክተው ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴዎቹና በሚቀርቡ ሪፖርቶች የተቀናጀ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ውጤታማ ስራዎች እንዲከናወኑ አድርጓል ብለዋል። በሌላ በኩል የፍርድ ቤቶችን የአደረጃጀት፣ የበጀት እና በዳኞች ሹመት ላይ ቁጥጥር በማድረግም ለፍትህ ስርአቱ ስኬት የበኩሉን መወጣቱን አንስተዋል። ምክር ቤቱ አስፈጻሚው አካል የህዝብን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የወጡ ህጎችና ደንቦች ከህገ መንግስቱ ጋር በተናበበ መልኩ ስራ ላይ መዋሉን ሲከታተል መቆየቱን አንስተዋል። የኢኮኖሚ ዘርፎች በተቀናጀ መንገድ እንዲተገበሩ ድጋፍ በማድረግም ለውጤቱም የድርሻውን ማበርከቱን አንስተዋል። በመጪው ሰኞ በሚካሄደው በ3ኛው የስራ ዘመን 5ኛው አመት 12ኛው መደበኛ ጉባኤውም የአስፈጻሚውንና የምክር ቤቱ ተጠሪ ተቋማትን የ2018 በጀት አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ይገመግማል ብለዋል። በተጨማሪ የ2019 በጀት አመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።
በምክር ቤቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች የውክልና ተሳትፎ ማደግ በሃሳብ ክርክር ላይ የተመሰረተ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ወሳኝ ነው
Jul 3, 2026 1934
አሶሳ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፡- በምክር ቤቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች የውክልና ተሳትፎ ማደግ በሃሳብ ክርክር ላይ የተመሰረተ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ላለፉት በርካታ ዓመታት በአንድ ገዥ ፓርቲ ፍጹም ቁጥጥር ስር የነበረና የተፎካካሪ ፓርቲዎች ሚና እጅግ የተገደበ የነበረበት መሆኑ ይታወቃል። በሀገሪቱ የመጣውን የፖለቲካ ለውጥ ተከትሎ በተካሄዱት ጠቅላላ ምርጫዎች ግን፣ የምርጫ ሥርዓቱን ነጻ፣ ገለልተኛና ታማኝ ለማድረግ በርካታ የህግና የተቋማት ማሻሻያዎች ተደርገዋል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም ቀደም ባሉት ምርጫዎች የነበረው የተፎካካሪ ፓርቲዎች ተሳትፎና የህዝብ ውክልና ዝቅተኛ የነበረ ቢሆንም፣ በሂደት በተደረጉ የፖለቲካ ሪፎርሞችና የውይይት መድረኮች ፓርቲዎች በነጻነት የመንቀሳቀስና አማራጭ ሃሳቦቻቸውን ለህዝብ የማቅረብ ዕድላቸው እያደገ መጥቷል። ይህ ውጤት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰላማዊ መንገድ የህዝብ ድምፅ አግኝተው የፖለቲካ ሥልጣን መጋራትና አማራጭ ሃሳብን ማሰማት የሚችሉበት ምህዳር እየተፈጠረ መሆኑን አመላካች ነው ተብሏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም የብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን መቀመጫ በመያዝ ያሸነፈ ሲሆን የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችም ከበፊቱ የተሻለ የክልል ምክርቤት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ አግኝተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንደተናገሩት፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ምህዳር እያደገ መምጣቱ የታየበት ነው። የቤኒሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ /ቤሕነን/ ፓርቲ ሊቀመንበር አብዱሰላም ሸንገል፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የነበረው የፖለቲካ ተሳትፎ ሀሳብ ብቻ ገዢ እና አሸናፊ የሆነበት ነው ብለዋል። ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ አካታች የሆነ የፖለቲካ ትርክትን መከተል እንደሚያስፈልግ ገልፀው፥ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች በሁሉም መስክ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። በቀጣይ በአሸናፊው የብልጽግና ፓርቲ የሚመሠረተው መንግሥት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ታሳቢ ማድረግ እንዳለበትና ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከመንግስት ጋር አብረው ለመስራት ዝግጁ ሊሆኑ እንደሚገባም ጠቁመዋል። ይህም የፖለቲካ ፓርቲዎችን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር እና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እንዲዳብር የሚያግዝ ነው ብለዋል። ፓርቲያቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች ማግኘቱን የተናገሩት አቶ አብዱሰላም፤ ከክልሉ መንግስት ጋር የጀመሩትን ትብብር በማጠናከር ለክልሉ ሰላምና ልማት በጋራ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጉሕዴን) ማዕከላዊ ኮሚቴ ፀሐፊ አቶ ለሜሳ ኔኖ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባገኘው መቀመጫ ከመንግሥት ጋር የበለጠ ተቀራርቦ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም የሁሉንም ህዝብ ድምጽ በመስማትና የበለጠ ሀገራዊ ሀላፊነት እንደተረከበ ከግምት ውስጥ በማስገባት በሙሉ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል።
በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችሉ ናቸው
Jul 3, 2026 1874
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው አሳታፊና አካታች ዐበይት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን በስልጡን የምክክር መፍትሔ ለመስጠት ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሰናድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ከሚቀጥለው ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሂደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤም ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። በአጀንዳዎቹም የሀገር ግንባታ፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደርና ሰላም ግንባታ ናቸው። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉትም፤ የሀገራዊ ምክክሩ ስምንት የዋናው ጉባኤ የምክክር ዐበይት አጀንዳዎች የኢትዮጵያን ወሳኝ ጉዳዮች የያዙ ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩም በዜጎች መካከል ለዘመናት የሚነሱ የአለመግባባት ሃሳቦችን በምክክር በመፍታት በሁሉም መስክ የጋራ የፖለቲካል ኢኮኖሚ አቅም መገንባት እንደሚያስችል ገልጸዋል። አስተያየት ሰጪዎች መካከል መቶ አለቃ ጋዲሳ አብዲ፤ የሀገራዊ ምክክሩ የህዝብ አሳታፊና አካታችነት በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን ለመገንባት ወሳኝ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። የዋናው ጉባኤ ቁልፍ አጀንዳዎችም የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት በማስቀጠል በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር እንደሚያስችሉ ገልጸዋል። ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ገዛኸኝ ደሜ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ የዘመናት ቅራኔን በውይይትና ስምምነት መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። በዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ስምንቱ ዐበይት አጀንዳዎችም የህዝብን ፍላጎቶችና ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ማሸጋገር እንደሚያስችሉ ተናግረዋል። የሀገራዊ ምክክሩ የህዝብ ተሳትፎና አካታችነት በመሰረታዊ የልማትና ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ መግባባትን በመፍጠር የጋራ ዕድገትን ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ አለው ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ለማ ወተሬ ናቸው። በዋናው የምክክር ጉባኤ የሚመክሩ የህዝብ ወኪሎችም ስልጡን ምክክር በማድረግ ለሀገርና ህዝብ የሚጠቅሙ መፍትሔዎችን ማፍለቅ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ወጣት ክብሬ አባረዳ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር በጋራ አስተሳሰብና ፍላጎት የምትገነባ ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ መሰረት ይጥላል ብሏል። በዐበይት አጀንዳነት የሚመከርባቸው ጉዳዮችም ከህዝብ የመነጩና ለሀገራዊ ዕድገትና ሰላም መግባባትን ለመገንባት የሚበጁ መሆናቸውን ገልጿል።
ፖለቲካ
ባገኘነው ዕውቀት ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በመጠቀም ሀገራችንን ለማገልገል ተዘጋጅተናል
Jul 5, 2026 390
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 28 /2018(ኢዜአ) ፦ያገኘነው ዕውቀት ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በተሻለ መንገድ እንድንረዳው አድርጎናል፤ ይህን ተጠቅመን ሀገራችንን ለማገልገል ተዘጋጅተናል ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ተመራቂዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተመራቂዎች አስመርቋል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመራቂዎች እንደገለጹት፤ በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ የተሰጣቸው ሥልጠና ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ስትራቴጂካዊ ዕይታን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። ከተመራቂዎቹ መካከል የኢፌዴሪ አየር ኃይል የ3ኛ አየር ምደብ ምክትል አዛዥ እና የተዋጊ ሄሊኮፕተር አብራሪና አስተማሪ ኮሎኔል ደረስ እንዳለ እንደገለጹት፤ በኮሌጁ ያካበቱት እውቀት ሀገሪቱ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን በግልጽ ለመረዳትና ለመተንተን የሚያስችል ከፍተኛ አቅም ፈጥሮላቸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ የምትገኝበት የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን ተለዋዋጭ ሁኔታ በውል ለመረዳት ማስቻሉን ገልጸው፤ ይህንን ስትራቴጂካዊ ዕይታ መሠረት በማድረግ ሀገራቸው የምትሰንቀውን ታላቅ ህልምና ግብ ለማሳካት በቁርጠኝነት ለመስራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል። ሌላው አስተያየታቸውን የሰጡት ከመከላከያ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ሌተናል ኮሎኔል ዶክተር ቴዎድሮስ ገብረ ሩፋኤል በበኩላቸው፤ በስትራቴጂክና ደኅንነት ጉዳዮች ላይ የተከታተሉት ትምህርት ዘርፈ-ብዙ ሁኔታዎችን በጥልቀት ለመተንተን ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን ጠቁመዋል። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ተለዋዋጭ ሁኔታዎች የበዙበት መሆኑን አመልክተው፤ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በትብብር መንፈስ የሚንቀሳቀሱ ከሆነ የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ በጎ ውጤት እንደሚያስገኙ አመልክተዋል። ሌላው ሰልጣኝ ከአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ የመጡት አቶ ጌታሰው ደሴ እንዳሉት፤ ሥልጠናው ለሀገር አንድነት፣ ለሀገር ፋይዳ እና ለተቋማት ግንባታ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ አስተዋጽኦ ለማበርከት ትልቅ አቅምና ወደፊት ለሚሰማሩበት የሥራ መስክም ስንቅ እንደሆናቸው ገልጸዋል። በተመሳሳይ ከልዩ ዘመቻዎች እዝ የመጡት ሌተናል ኮሎኔል ደረጀ ዳባሳ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ያገኙት ዕውቀት የእለት ተእለት ተግባራቸውና ከሙያቸው ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ ስትራቴጂካዊ አካባቢውን፣ ጂኦፖለቲካውን እና አጠቃላይ ሁኔታውን በተገቢው መንገድ ለመረዳት አስችሏቸዋል። ትምህርቱ ለተግባራዊ ስራቸው ጠንካራ መነሻ ከመሆኑም በላይ፣ ባላቸው የረጅም ጊዜ ልምድ ላይ ትልቅ አቅም የገነባ መሆኑንም አክለዋል። የኮሌጁ ሰልጣኝ የሆኑት ኮሎኔል እማምር አያሌው በበኩላቸው፤ ቀጣናዊና የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ በደንብ በመረዳት መተንተን የሚችል ጠንካራ ሰራዊት እየተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም በአስተሳሰብ የበሰለ፣ በስትራቴጂካዊ እውቀት የዳበረና ለማንኛውም ሀገራዊ ግዳጅ ዝግጁ የሆነ ሠራዊት መገንባቱን ጠቁመዋል፡፡
ህዝቡ አሉታዊ የሆኑ የውስጥ እና የውጭ ተጽዕኖዎች ሳይበግሩት በምርጫው ያሳየው ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ የሚደነቅ ነው-የጋራ ምክር ቤቱ
Jul 5, 2026 468
አዲስ አበባ፤ሰኔ 28/ 2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ህዝብ አሉታዊ የሆኑ የውስጥ እና የውጭ ተጽዕኖዎች ሳይበግሩት በምርጫው ያሳየው ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ ገለፁ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደትን አስመልክቶ ውይይት አድርጓል። ምክር ቤቱ በጉባኤው ከተወያየባቸው ጉዳዮች መካከል የፖለቲካ ፓርቲዎች ከ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ስለሚወስዱት ትምህርትና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ይገኙበታል። እንዲሁም የሂደቱ ተዓማኒነት እና አካታችነትን በተመለከተ በቀጣይ ምን መደረግ እንዳለበት እና በጋራ መፍትሄዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። የጉባኤው ተሳታፊዎችም ህዝቡ አሉታዊ የሆኑ የውስጥ እና የውጭ ተጽእኖዎች ሳይበግሩት ያሳየው ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን አቶ ሰለሞን አየለ ለኢዜአ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁ በውይይቱ ላይ ተገልጿል። ለዚህም ስኬት የበኩላቸውን ሃላፊነት ለተወጡ የፀጥታና የደህንነት አካላት፤ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ፣ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የጋራ ምክር ቤቶች አመራሮች እና ሌሎች አካላት የጋራ ምክር ቤቱ ምስጋና ያቀርባል ብለዋል።
ለውይይት የቀረቡት አጀንዳዎች ዘመናትን ለተሻገሩ አለመግባባቶች ዘላቂ መፍትሔን በመስጠት የኢትዮጵያን መጻኢ ጉዞ የሚወስኑ ናቸው
Jul 5, 2026 366
ሀዋሳ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለምክክር ጉባኤው ያዘጋጃቸው ስምንቱ አጀንዳዎች፣ ዘመናትን ለተሻገሩ አለመግባባቶች ዘላቂ መፍትሔን በመስጠት የኢትዮጵያን መጻኢ ጉዞ የሚወስኑ መሆናቸውን የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ገለጸ። ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት አሳታፊ በሆነ መንገድ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሰበሰባቸውን አጀንዳዎች መነሻ በማድረግ፣ ከሐምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሄደው ዋና የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ ስምንት አጀንዳዎችን ለይቶ አቅርቧል፡፡ በጉባኤው አጀንዳዎች ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረገው የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወጣት በቃሉ መሰረት፤ ኮሚሽኑ ባለፉት ዓመታት አሳታፊ በሆነ መልኩ አጀንዳዎችን የማሰባሰብ ሥራ ማከናወኑን ገልጿል። ሂደቱ በርካታ ምዕራፎችን አልፎ ለዚህ መብቃቱን ያደነቀው ወጣት በቃሉ፣ ለዋናው የምክክር ጉባኤ የተለዩት አጀንዳዎች ዘመናትን ለተሻገሩ አለመግባባቶች ዘላቂ መፍትሔ በመስጠት የኢትዮጵያን መጻኢ ጉዞ የሚወስኑ መሆናቸውን ጠቁሟል። በአጀንዳዎቹ ላይ በጥልቀት በመወያየት ለችግሮቹ ዘላቂ መፍትሔን መሻት እንደሚገባ ጠቅሶ፣ ይህንን ወርቃማ ዕድል ማባከን እንደማይገባና ሂደቱ ፍሬያማ እንዲሆን ሁሉም ዜጋ የሚጠበቅበትን እንዲወጣም አሳስቧል፡፡ የማህበሩ አባል የሆነችው ወጣት በረከት ጴጥሮስ በበኩሏ፤ የሀገርን ልማትና ሰላም ለማስቀጠል ልዩነቶችን በውይይትና በንግግር መፍታት ወቅቱ የሚጠይቀው የሰለጠነ መንገድ መሆኑን ተናግራለች፡፡ ኮሚሽኑ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ልዩነት የፈጠሩና የግጭት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት የጋራ መግባባትን ለመፍጠር ያዘጋጃቸው አጀንዳዎች ዘላቂ ሰላምን የሚያመጡና ጠንካራ ሀገርን የሚፈጥሩ መሆናቸውን ገልጻለች፡፡ እንደ ሀገር የተፈጠሩ ልዩነቶችንና ለግጭት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በምክክር ለመፍታት የሚደረገው ጥረት ለኢትዮጵያውያን ትልቅ ዕድል መሆኑን የገለጸው ደግሞ የክልሉ ወጣቶች ማህበር ሥራ አስፈጻሚ ወጣት አሸናፊ ኤፍሬም ነው፡፡ ኮሚሽኑ ለምክክር ጉባኤው የለያቸው አጀንዳዎች ለበርካታ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡና የበለጸገች ሀገርን ለትውልድ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ተናግሯል፡፡ ኮሚሽኑ ከዋናው ጉባኤ በፊት በየደረጃው ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ሲያደርግ የነበረው ውይይት በጠረጴዛ ዙሪያ የመነጋገር ባህልን ማሳደጉን የጠቀሰው ወጣት አሸናፊ፣ ምክክሩ የታለመለትን ውጤት እንዲያመጣ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባም ጥሪውን አስተላልፏል።
የሰላም ጥሪ በመቀበል ከጥፋታችን ተምረን ለልማትና ሰላም ግንባታ አርአያ በመሆን እየሰራን ነው-የቀድሞ ታጣቂዎች
Jul 5, 2026 422
ደብረ ብርሃን፤ሰኔ 28/ 2018(ኢዜአ)፡- የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ከጥፋታችን ተምረን ለልማትና ለሰላም ግንባታ አርአያ በመሆን እየሰራን ነው ሲሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ገለጹ። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ህብረተሰቡን ተቀላቅለው በልማት ስራ ላይ የተሰማሩ የቀድሞ ታጣቂዎችን የኢዜአ ሪፖርተር አነጋግሯቸዋል። ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል አጎላላና ጠራ ወረዳ የሚኖረው አወቀ ስለሺ፤ በተሳሳተ መንገድ ጫካ በመግባት ማህበረሰቡንም ይሁን ቤተሰቡን የጎዱበት አጋጣሚ ሲያስታውስ ከፍተኛ ጸጸት የሚሰማው መሆኑን ገልጿል። በጫካ እንዲሰባሰቡ ያደረጓቸው አካላት ለዘረፋና ሃብት ማካበት የተሰለፉ መሆኑን በመረዳቱ የመንግስትን የሰላም ጥሪ መቀበሉን ተናግሯል። ከስልጠና በኋላ በተደረገለት የገንዘብ ድጋፍና በተሰጠው የመስሪያ ቦታ ወደ ልማት በመግባት ከራሱም አልፎ ቤተሰቡንና ማህበረሰቡን የሚጠቅም ተግባር ላይ መሰማራቱን ገልጿል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ከጥፋታችን ተምረን ለልማትና ለሰላም ግንባታ አርአያ በመሆን እየሰራን እንገኛለን፤ ይህንንም አጠናክረን እንቀጥላለን ሲል ተናግሯል። በመሆኑም በጫካ የሚገኙ ወጣቶች ይህንን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከጥፋት በመውጣት የልማትና የሰላም አርአያ ለመሆን እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። ሌላኛው የቀድሞ ታጣቂ ሚኪያስ ቸርነት፤ በተሳሳተ መልኩ ወደ ጫካ በመግባት በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ በፈፀመው በደል መፀፀቱን ገልጿል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል በተደረገለት ድጋፍ ወደ ልማት በመግባት ሰላማዊ ህይወት በመምራት ላይ መሆኑን ተናግሯል። በጠመንጃ ትግል ከጥፋት በስተቀር የሚመጣ አንዳችም ውጤት የሌለ መሆኑን በመረዳት ሰላምና ልማትን በመምረጥ እየሰራ መሆኑን ገልፆ፤ ሌሎች በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎችም ከተሳሳተ መንገዳቸው እንዲመለሱ አስገንዝቧል። በሰሜን ሸዋ ዞን የአጎለላና ጠራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አዳፍሬ ማንደፍሮ፤ የመንግስት የሰላም ጥሪ ብዙዎቹን ወደ ሰላማዊ ህይወት እየመለሳቸውና ሰርተውም እየተለወጡ መሆኑን ገልጸዋል። በጫካ የሚገኙ ሌሎች ታጣቂዎችም እየሄዱበት ያለው መንገድ የተሳሳተ እና ማህበረሰብን የሚጎዳ መሆኑን በመገንዘብ ጊዜ ሳያባክኑ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እንዲመጡ መልእክት አስተላልፈዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ምክትል ሃላፊ ዓባይ ዲሌ፤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን የመቀበልና በዘላቂነት የማቋቋም ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ በፊት የተመለሱት በተለያዩ የልማት መስኮች ተሰማርተው እየሰሩ ስኬታማ መሆናቸውን አንስተው፥ ሌሎች በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎችም የእነርሱን ፈለግ በመከተል እንዲመጡ ጥሪ አቅርበዋል። የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው የሚመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችን ለመደገፍና በዘላቂነት ለማቋቋም መንግስት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። በሰሜን ሸዋ ዞንና አካባቢው ያለውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት በተለይም የሃገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና አጠቃላይ ማህበረሰቡ የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
መከላከያ ሠራዊት የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት እየጠበቀ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Jul 4, 2026 1894
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት በአስተማማኝነት እየጠበቀ መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተመራቂዎች አስመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላምና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር)፣ የኮሌጁ አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ጥላሁን ደምሴ እና ከፍተኛ ጄኔራል መኮንኖች ተገኝተዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሥነ-ስርዓቱ ባስተላለፉት፤ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ የደህንነት ሁኔታ ውስብስብና ኢ-ተገማችነትን ታሳቢ ያደረገ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ቀጣናዊ የትብብር መርህ ለማደናቀፍ የታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች የሴራ ጥምረት ወይም "ፅምዶ" ፈጥረው እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊ ሰላምና ደህንነት በመጠበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለዘመናት በሰላም እጦት የሚገለፀው የቀይ ባሕርና አፍሪካ ቀንድ አከባቢ የደህንነት ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ እየተወሳሰበ መምጣቱን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው የምትገኝ፣ ከማንኛውም የቀጣናው ችግርና ተጠቃሚነት ማምለጥ የማትችል ትልቅ ሀገር መሆኗንም አስገንዝበዋል። ታሪካዊ ጠላቶችም ኢትዮጵያ ቀጣናውን የማረጋጋት የመሪነት ሚና እንዳትወጣና በውስጥ ጉዳዮች ብቻ እንድትጠመድ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በሌላ በኩልም ጎረቤቶችን እንዲታመሱ በማድረግ ለውስጣዊ ደህንነታችን ጫና መፍጠር የሚችሉ ሴራዎችን በመሸረብ ቀጣናውን ለማተራመስ አበክረው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ከባሕር ዳርቻ ለማስወጣት የተጠቀሙበት የረጅም ዘመናት ሴራም ዛሬ ላይ ፅምዶ በሚል ስያሜ ዕድሳት ተደርጐለት እየተስተጋባ ነው ብለዋል። የዘመኑ ጦርነት በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በረጅም ርቀት ሚሳኤሎች፣ በሰው አልባ መሣሪያዎችና በሳይበር ኦፕሬሽኖች የታገዘ የቴክኖሎጂ ጦርነት መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትም አደረጃጀቱንና ዘመናዊ ትጥቁን በማጠናከር በማንኛውም አስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ቁመና ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ተመራቂዎችም የቀሰሙትን ስትራቴጂክ ዕውቀት ለሠራዊቱ ተጨማሪ ግንባታ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አሳስበዋል። የኮሌጁ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ጥላሁን ደምሴ በበኩላቸው፤ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት የተመሰረተው ኮሌጁ በተለዋዋጭ ስትራቴጂክ ምህዳር ውስጥ የብሔራዊ ኃይል ማስፈፀሚያ አቅሞችን ውጤታማ ለማድረግ እየሰራ ነው ብለዋል። ኮሌጁ የስርዓተ ትምህርት ማሻሻያ በማድረግ በጥናት፣ ምርምርና የደህንነት ትንተና ላይ ትኩረት አድርጎ የአመራር አቅም ግንባታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል። መንግሥት የኮሌጁን የመሰረተ ልማትና የዲጂታላይዜሽን አቅም በማሳደግ ወደ ስማርት ኮሌጅ ለመቀየር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የአስተዳደሩ ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላትን ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት ተገኝቷል
Jul 3, 2026 2092
ድሬደዋ፤ ሰኔ 26/2018(ኢዜአ)፦) የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የአስፈጻሚውን አካላት ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት መገኘቱን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አፈጉባኤ አብዲ ሙክታር ገለጹ። ምክር ቤቱ የስራ ዘመኑን መደበኛ ጉባኤ የፊታችን ሰኞ ያካሂዳል። የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር፣ ምክር ቤቱ የአስፈፃሚውን አካላት የአምስት አመታት የስራ እቅድና አፈጻጸም የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን አስመልክተው ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴዎቹና በሚቀርቡ ሪፖርቶች የተቀናጀ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ውጤታማ ስራዎች እንዲከናወኑ አድርጓል ብለዋል። በሌላ በኩል የፍርድ ቤቶችን የአደረጃጀት፣ የበጀት እና በዳኞች ሹመት ላይ ቁጥጥር በማድረግም ለፍትህ ስርአቱ ስኬት የበኩሉን መወጣቱን አንስተዋል። ምክር ቤቱ አስፈጻሚው አካል የህዝብን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የወጡ ህጎችና ደንቦች ከህገ መንግስቱ ጋር በተናበበ መልኩ ስራ ላይ መዋሉን ሲከታተል መቆየቱን አንስተዋል። የኢኮኖሚ ዘርፎች በተቀናጀ መንገድ እንዲተገበሩ ድጋፍ በማድረግም ለውጤቱም የድርሻውን ማበርከቱን አንስተዋል። በመጪው ሰኞ በሚካሄደው በ3ኛው የስራ ዘመን 5ኛው አመት 12ኛው መደበኛ ጉባኤውም የአስፈጻሚውንና የምክር ቤቱ ተጠሪ ተቋማትን የ2018 በጀት አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ይገመግማል ብለዋል። በተጨማሪ የ2019 በጀት አመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።
በምክር ቤቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች የውክልና ተሳትፎ ማደግ በሃሳብ ክርክር ላይ የተመሰረተ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ወሳኝ ነው
Jul 3, 2026 1934
አሶሳ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፡- በምክር ቤቶች የፖለቲካ ፓርቲዎች የውክልና ተሳትፎ ማደግ በሃሳብ ክርክር ላይ የተመሰረተ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ላለፉት በርካታ ዓመታት በአንድ ገዥ ፓርቲ ፍጹም ቁጥጥር ስር የነበረና የተፎካካሪ ፓርቲዎች ሚና እጅግ የተገደበ የነበረበት መሆኑ ይታወቃል። በሀገሪቱ የመጣውን የፖለቲካ ለውጥ ተከትሎ በተካሄዱት ጠቅላላ ምርጫዎች ግን፣ የምርጫ ሥርዓቱን ነጻ፣ ገለልተኛና ታማኝ ለማድረግ በርካታ የህግና የተቋማት ማሻሻያዎች ተደርገዋል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም ቀደም ባሉት ምርጫዎች የነበረው የተፎካካሪ ፓርቲዎች ተሳትፎና የህዝብ ውክልና ዝቅተኛ የነበረ ቢሆንም፣ በሂደት በተደረጉ የፖለቲካ ሪፎርሞችና የውይይት መድረኮች ፓርቲዎች በነጻነት የመንቀሳቀስና አማራጭ ሃሳቦቻቸውን ለህዝብ የማቅረብ ዕድላቸው እያደገ መጥቷል። ይህ ውጤት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰላማዊ መንገድ የህዝብ ድምፅ አግኝተው የፖለቲካ ሥልጣን መጋራትና አማራጭ ሃሳብን ማሰማት የሚችሉበት ምህዳር እየተፈጠረ መሆኑን አመላካች ነው ተብሏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም የብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን መቀመጫ በመያዝ ያሸነፈ ሲሆን የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችም ከበፊቱ የተሻለ የክልል ምክርቤት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ አግኝተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንደተናገሩት፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ምህዳር እያደገ መምጣቱ የታየበት ነው። የቤኒሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ /ቤሕነን/ ፓርቲ ሊቀመንበር አብዱሰላም ሸንገል፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የነበረው የፖለቲካ ተሳትፎ ሀሳብ ብቻ ገዢ እና አሸናፊ የሆነበት ነው ብለዋል። ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ አካታች የሆነ የፖለቲካ ትርክትን መከተል እንደሚያስፈልግ ገልፀው፥ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች በሁሉም መስክ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። በቀጣይ በአሸናፊው የብልጽግና ፓርቲ የሚመሠረተው መንግሥት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ታሳቢ ማድረግ እንዳለበትና ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከመንግስት ጋር አብረው ለመስራት ዝግጁ ሊሆኑ እንደሚገባም ጠቁመዋል። ይህም የፖለቲካ ፓርቲዎችን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር እና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እንዲዳብር የሚያግዝ ነው ብለዋል። ፓርቲያቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች ማግኘቱን የተናገሩት አቶ አብዱሰላም፤ ከክልሉ መንግስት ጋር የጀመሩትን ትብብር በማጠናከር ለክልሉ ሰላምና ልማት በጋራ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጉሕዴን) ማዕከላዊ ኮሚቴ ፀሐፊ አቶ ለሜሳ ኔኖ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባገኘው መቀመጫ ከመንግሥት ጋር የበለጠ ተቀራርቦ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም የሁሉንም ህዝብ ድምጽ በመስማትና የበለጠ ሀገራዊ ሀላፊነት እንደተረከበ ከግምት ውስጥ በማስገባት በሙሉ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል።
በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው ዐበይት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችሉ ናቸው
Jul 3, 2026 1874
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚመከርባቸው አሳታፊና አካታች ዐበይት አጀንዳዎች ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የዘለቁ አለመግባባቶችን በስልጡን የምክክር መፍትሔ ለመስጠት ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ለዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሰናድተዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ከሚቀጥለው ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚያካሂደው ዋናው ሀገራዊ ጉባኤም ስምንት ዐበይት አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። በአጀንዳዎቹም የሀገር ግንባታ፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደርና ሰላም ግንባታ ናቸው። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉትም፤ የሀገራዊ ምክክሩ ስምንት የዋናው ጉባኤ የምክክር ዐበይት አጀንዳዎች የኢትዮጵያን ወሳኝ ጉዳዮች የያዙ ናቸው። ሀገራዊ ምክክሩም በዜጎች መካከል ለዘመናት የሚነሱ የአለመግባባት ሃሳቦችን በምክክር በመፍታት በሁሉም መስክ የጋራ የፖለቲካል ኢኮኖሚ አቅም መገንባት እንደሚያስችል ገልጸዋል። አስተያየት ሰጪዎች መካከል መቶ አለቃ ጋዲሳ አብዲ፤ የሀገራዊ ምክክሩ የህዝብ አሳታፊና አካታችነት በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን ለመገንባት ወሳኝ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። የዋናው ጉባኤ ቁልፍ አጀንዳዎችም የሀገርን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት በማስቀጠል በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር እንደሚያስችሉ ገልጸዋል። ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ገዛኸኝ ደሜ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ የዘመናት ቅራኔን በውይይትና ስምምነት መፍትሔ መስጠት የሚያስችል ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። በዋናው ጉባኤ የሚመከርባቸው ስምንቱ ዐበይት አጀንዳዎችም የህዝብን ፍላጎቶችና ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ማሸጋገር እንደሚያስችሉ ተናግረዋል። የሀገራዊ ምክክሩ የህዝብ ተሳትፎና አካታችነት በመሰረታዊ የልማትና ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ መግባባትን በመፍጠር የጋራ ዕድገትን ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ አለው ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ለማ ወተሬ ናቸው። በዋናው የምክክር ጉባኤ የሚመክሩ የህዝብ ወኪሎችም ስልጡን ምክክር በማድረግ ለሀገርና ህዝብ የሚጠቅሙ መፍትሔዎችን ማፍለቅ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ሌላኛው የመዲናዋ ነዋሪ ወጣት ክብሬ አባረዳ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር በጋራ አስተሳሰብና ፍላጎት የምትገነባ ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ መሰረት ይጥላል ብሏል። በዐበይት አጀንዳነት የሚመከርባቸው ጉዳዮችም ከህዝብ የመነጩና ለሀገራዊ ዕድገትና ሰላም መግባባትን ለመገንባት የሚበጁ መሆናቸውን ገልጿል።
ማህበራዊ
በአማራ ክልል የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው
Jul 5, 2026 210
ጎንደር ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ባለፉት ዓመታት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን የአማራ ክልል ሴቶች፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ በጎንደር ከተማ አካሄዷል። የቢሮ ኃላፊዋ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው። ለአብነትም በበጀት ዓመቱ በባህር ዳርና ደብረ ማርቆስ ከተሞች ከ266 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። የገበያ ማዕከላቱም ተደራጅተውና በግል የሙያ ዘርፎች የስራ ዕድል ለሚፈጠርላቸው ሴቶች የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ችግርን ለመቅረፍ የሚያስችሉ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም የማዕከላቱ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅም ለ100 ሴቶች ቋሚ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ እንዲያገኙ ዕድልን እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል። በገቢ ማስገኛ ፕሮግራሞች፣ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ የሴቶችንና የህጻናትን መብት በማስጠበቅና በሌሎች ተያያዥ ተግባራት የተጀመሩ ስራዎች በአዲሱ በጀት ዓመት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሴቶች፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ቀኑ ቢያድጎ በበኩላቸው፣ በበጀት ዓመቱ ለ33 ሺህ ሴቶች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረ ገልጸዋል። በተጨማሪም ሰባት የህፃናት ማቆያዎችን በማስገንባት የሚያጠቡ እናቶች ልጆቻቸውን በቅርበት እየተከታተሉ መደበኛ ስራቸውን በትጋት እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎትም አቅመ ደካሞችን፣ ህጻናትን፣ የአካል ጉዳተኞችንና ሌሎች ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመደገፍ ስራ መሰራቱን አስረድተዋል። "ያለዕድሜ ጋብቻን ጨምሮ ከሌሎች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች ነጻ የሆኑ 25 ቀበሌዎች ተፈጥረዋል" ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ አስተዳደር የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉቀን ጌታሁን ናቸው። በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ በተለያየ ምክንያት ለተቸገሩ 64 ሴቶች ከክልሉ በተገኘ 6 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ድጋፍ የማቋቋም ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በዕለቱም በጎንደር ከተማ የተገነባውን የሴቶችና ህጻናት የተሃድሶ ማዕከል ወደ ስራ የማስገባት ተግባር ተከናውኗል።
ተመራቂ እጩ መምህራን በስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ሙያዊ ሃላፊነት አለባቸው
Jul 5, 2026 221
ሰቆጣ ፤ሰኔ 28/2018(ኢዜአ)፡- ተመራቂ እጩ መምህራን በስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ሙያዊ ሃላፊነታቸውን መወጣት አለባቸው ሲሉ የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ ገለፁ። የሰቆጣ መምህራን ኮሌጅ በዲግሪና በዲፕሎማ ደረጃ ያስተማራቸውን 484 እጩ መምህራንን በዛሬው እለት አስመርቋል። በምረቃው ላይ የተገኙት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ በወቅቱ፤ ሀገራችን ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ የትምህርት ዘርፉ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ብለዋል። ተተኪው ትውልድ የተማረና በፈጠራ ክህሎት የዳበረ እውቀት እንዲገነባ ለማስቻል መምህራን ያላቸው ድርሻም የላቀ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ተመራቂ እጩ መምህራን ሀገር አሻጋሪና በስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ሙያዊ ሃላፊነት አለባችሁ ብለዋል። የሰቆጣ መምህራን ኮሌጅ ዲን ወርቁ ጌጡ እንዳሉት ኬሌጁ ዕጩ መምህራንን በመደበኛና በክረምት መርሃ ግብሮች በማስተማር ለትምህርት ስርዓቱ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል። በዘንድሮው ዓመትም በዲግሪና በዲፕሎማ ደረጃ ያስተማራቸውን 484 እጩ መምህራንን በዛሬው እለት ማስመረቁን አስረድተዋል። በዛሬው እለት ካስመረቃቸው መካከል ኮሌጁ ለመጀመሪያ ጊዜ በኽምጣኟ ቋንቋ በዲግሪ መርሃግብር ያስተማራቸው ዕጩ መምህራን ይገኙበታል ብለዋል። ዕጩ መምህራን የተማረ ዜጋ ለመቅረፅና በፈጠራ የበለፀገ ትውልድ እንዲፈጠር የሙያ ግዴታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በዲግሪ መርሃ ግብር ተመራቂ ዕጩ መምህር ወርቄ ደሳለኝ እንዳሉት በኮሌጁ ባገኙት እውቀት በራስ የሚተማመን የተማረ ዜጋ ለመፍጠር ሙያዊ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ዕጩ መምህር ኪሮስ ተክሌ በበኩላቸው በተማሩት የመምህርነት ሙያ በፈጠራ የበለፀገና የተማረ ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ርብርብ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።
የሐረሪ ባህልና ስፖርት ፌስቲቫል በአሜሪካዋ ሜምፊስ ከተማ እውቅና አገኘ
Jul 5, 2026 229
አዲስ አበባ፤ሰኔ 28/ 2018(ኢዜአ):-በአሜሪካዋ ሜምፊስ ከተማ የሐረሪ ባህልና ስፖርት ፌስቲቫል የከተማዋ በዓል ሆኖ እንዲከበር የከተማው ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ ወስኗል። በከተማው የሀረሪ ማህበረሰብ በየአመቱ የሚያከብሩት የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል አከባበር እውቅና ማግኘቱ ባህሎቻቸውን፣ታሪኮቻቸውንና እሴቶቻቸውን ለሌላው ማህበረሰብ በላቀ ደረጃ ለማስተዋወቅ እንደሚያስችል ተጠቅሷል። እውቅናው ከዚህ በተጨማሪም በተለያዩ አለማት ለሚገኙ የሐረሪ ማህበረሰብ ትልቅ ኩራት ከመሆኑ ባሻገር የጥንታዊ ባህሎቻቸውን ጠብቆ ለማቆየትና ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ትልቅ መነሳሳትን የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል። የከተማዋ ምክር ቤት የሰጠው እውቅናም ከተማዋ ለባህል ብዝሃነት፣ለህዝቦች የእርስ በእርስ ትውውቅና ትስስር እንዲጠናከር ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ተመላክቷል። እንዲሁም በሜምፊስና በሐረር ከተሞች መካከል የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ተጠቁሟል። በዓሉም በየአመቱ July 1 ቀን እንዲከበር ምክር ቤት በአዋጅ ደንጓል።
በክልሉ በትምህርት ዘመኑ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተከናወኑ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል
Jul 5, 2026 251
ሆሳዕና ፤ ሰኔ 28/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ 2018 የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ትምሀርት ቢሮ ገለፀ። በክልሉ የትምህርት ሴክተር የ 2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀምና የ2019 የቅድመ ዝግጅትና የክረምት ስራዎች ዙሪያ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ በ 2018 የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ። የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል እና ጥራት ያለው ትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት ትኩረት ተደርጎ ሲመራ መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡ ማህበረሰቡን በማሳተፍ ትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ ማድረግ፣ የትምህርት ቤቶችን ጀረጃ ማሻሻል፣ የትምህርት ግብዓት ማሟላትና መሰል ተግባር በስፋት የተከናወኑ ተግባራት መሆናቸውን ደግሞ ለአብነት አንስተዋል፡፡ በትምህርት ዘመኑ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ በክልሉ የተጀመሩ ስራዎች ውጤት ስለማምጣታቸው አንስተው፤ ስራዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የትምህርት አመራሩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበትም ነው ያስገዘቡት። በመድረኩ ተሳታፊ ከሆኑት መካከል የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ሃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም፤ በዞኑ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ከ612 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ስራ ሲተገበር ቆይቷል ብለዋል። በዚህም የበርካታ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል ስለመቻሉ አንስተው፤ በዘርፉ በመመዝገብ ላይ የሚገኘው ስኬት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልጸዋል። የሀድያ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ዴታሞ ጡምደዶ በበኩላቸው እንደገለፁት፤ ዘመኑ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመቀናጀት የማጠናከሪያ ትምህርት ሲሰጥ የቆዩበት መሆኑን ጠቁመዋል። በዞኑ በ 80 ትምህርት ቤቶች የምገባ መርሐ ግብር በማካሄድ የመጠነ ማቋረጥ ችግር የመቅረፍና ተማሪዎች ተረጋግተው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻሉን ጠቅሰው፤ ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው የገለፁት።
ኢኮኖሚ
የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል ተችሏል- አቶ ሽመልስ አብዲሳ
Jul 5, 2026 400
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በበጀት ዓመቱ የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል መቻሉን የፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ። አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዳሉት በ2018 በጀት ዓመት በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማትንና የዜጎችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል። የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ክፍፍል ሥርዓት በጥናትና በተደራጀ ዕቅድ እንዲመራ ከማድረግ ባሻገር ወደ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚተላለፉ ሀብቶች ግልጽና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲከፋፈሉ ክትትልና ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል መቻሉን ገልጸዋል። ይህም የሚተላለፉ ሀብቶች ላይ ግልጽነትን ለማሳደግና የበይነ መንግሥታት የፊስካል ሽግግር ሥርዓትን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አብራርተዋል። በተጨማሪም የፌዴራል መሠረተ ልማት ስርጭት ፍትሐዊነትን ማስፈን እንዲሁም ልዩ ዓላማ ያላቸው ድጎማዎች በግልጽነትና በተጠያቂነት መርህ ለክልሎች መከፋፈላቸውን ማረጋገጥ የኮሚቴው ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ተግባራት እንደነበሩ አመልክተዋል። የኢኮኖሚና የማሕበራዊ ዕድገትን ማፋጠንና በክልሎች መካከል ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ የረጅም ጊዜ ጥረት እንደሚጠይቅ ገልጸው ማነቆዎችን በመለየትና መረጃዎችን በወቅቱ በማሰባሰብ ዘላቂ መፍትሔዎችን ለማምጣት ይሰራል ማለታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት መረጃ ያመለክታል።
በክልሉ የምርት ግብዓት ቁጥጥርን በማጠናከር ምርታማነትን ለማላቅ በተከናወነ ተግባር ውጤት ተገኝቷል
Jul 5, 2026 187
ባህርዳር፤ ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የእርሻ ምርት ግብዓት ቁጥጥርን በማጠናከር ምርታማነትን ለማላቅ በተከናወነ ተግባር ውጤት መገኘቱን የክልሉ የግብርና ጥራትና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታወቀ። የክልሉ የግብርና ጥራትና ቁጥጥር ባለሥልጣን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድና አፈፃፀም መድረክን በባህር ዳር ከተማ ዛሬ አካሄዷል። በወቅቱም የአማራ ክልል የግብርና ጥራትና ቁጥጥር ባለሥልጣን ኃላፊ አቶ ፈንታሁን ስጦታው እንደገለጹት፤ ባለሥልጣኑ በዘር፣ በማዳበሪያ፣ በፀረ-አረም ኬሚካል፣ በመጤ አረምና በሌሎች የግብርና ግብዓቶች ላይ የጥራትና ቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ይገኛል። በዚህም በክልሉ የእርሻ ምርት ግብዓት ቁጥጥርን በማጠናከር ምርታማነትን ለማላቅ በተከናወነ ተግባር ውጤት ተገኝቷል ብለዋል። ለአብነትም በበጀት ዓመቱ ከ10 ሺህ 800 ሄክታር በላይ በምርጥ ዘር በተሸፈነ መሬት ላይ ቁጥጥር በማድረግ፣ ከ600 ሄክታር በላይ የተዘራው ዘር የጥራት ደረጃውን ባለማሟላቱ ውድቅ መደረጉን አንስተዋል። በተለይም በመሰብሰብ፣ በማከማቸት፣ በማጓጓዝና በማሰራጨት ላይ የሚከሰትን የጥራት መጓደል ለመቀነስ ለባለድርሻ አካላት ሰፊ ግንዛቤ ተፈጥሮ ወደ ሥራ በመገባቱ አበረታች ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ግብርና ጥራትና ቁጥጥር ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ብርሃኔ ገብሬ በበኩላቸው ሥራው በምሥራቅ አማራ በሚገኙ በዋግ ኸምራና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደሮች፣ በሰሜንና በደቡብ ወሎ ዞኖች ላይ በማተኮር መሠራቱን ገልጸዋል። በነዚህ ዞኖች በዘር ብዜት ላይ የተሰማሩ ስምንት ድርጅቶች ላይ ከማሳ ጀምሮ ተገቢውን የዘር ጥራትና ቁጥጥር በማድረግ፣ ከ20 ሺህ ኩንታል በላይ ጥራቱን የጠበቀ ምርጥ ዘር ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል። በቀጣይም የግብዓት ጥራት፣ ደህንነትና ቁጥጥር ተግባሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመረው ቅንጅታዊ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በውይይቱ ላይ የተገኙት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አጀበ ስንሻው በክልሉ ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ ለወጪ ንግድና ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆን ምርት ለማምረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። ጥራቱ የተረጋገጠ ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያና ሌሎች ግብዓቶችን ለአርሶ አደሩና ለባለሀብቱ በወቅቱ ማቅረብ ለግብርናው ዘርፍ ምርታማነት ማደግ መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የሚመረተውን ምርጥ ዘር ወደ ውጭ ለመላክና ለማስገባት፣ በሥርዓተ ምግብ በኩልም የሰውን ጤና የማይጎዳ ምርት ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ ለማቅረብ እንደሚያስችል አስረድተዋል። በዚህም ባለሥልጣኑ የግብርና ግብዓትን ጥራት በማሳ ላይና በላቦራቶሪ በመመርመር እንዲሁም የላቀ ቁጥጥር በማድረግ እያከናወነ ያለው ሥራ የሚበረታታ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል። በመድረኩ ላይ የባለሥልጣኑ እና የዞን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የሀዋሳ ከተማ የኮሪደርና የሀይቅ ዳርቻ ልማት የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ እያራዘመ ነው
Jul 5, 2026 206
ሀዋሳ ፤ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ) :- የሀዋሳ ከተማ የኮሪደርና የሀይቅ ዳርቻ ልማት የጎብኚዎችን ቀልብ በመሳብ የቆይታ ጊዜያቸውን እያራዘመው እንደሚገኝ የሲዳማ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ገለጸ። በሲዳማ ክልል ታሪካዊና የተፈጥሮና የቱሪስት መስህቦችን በማልማትና በማስተዋወቅ ረገድ በተሰራው ሥራ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ3 ሚሊዮን 280 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጪ ቱሪስቶች ክልሉን መጎብኘታቸውን ቢሮው ገልጿል። የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊ አቶ አበበ ማሪሞ ለኢዜአ እንደገለፁት የቱሪስት መስህቦችን በማልማት ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን ለማጉላት ሰፊ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ። ለዚህም በአብነትነት የሀዋሳ ፍቅር ሐይቅን፣ የጋራንባ ተራራ ባህላዊ ሎጅን፣ የሲዳማ አፊኒ ሶንጎ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓት ማከናወኛ ስፍራን፣ የተፈጥሮ ፍል ውኃ ስፍራዎችንና ፏፏቴዎችን ጠቅሰዋል። በተለይም የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማትና የሐይቅ ዳርቻ ልማት የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ እንዲጨምር ማድረጉን አቶ አበበ አንስተዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ክልሉን ከ3 ሚሊዮን 280 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች መጎብኘታቸውንና ከዚህም 3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል። ከአዲስ አበባ ሀዋሳን ለመጎብኘት የመጡት አቶ ዘላለም ተስፋዬ በሰጡት አስተያየት፤ የሀዋሳ ከተማ ዕድገት፣ የኮሪደር ልማቱና የሐይቅ ዳርቻ ማሻሻያው የቱሪስቶችን ቀልብ መሳብ የሚችሉና ከተማዋን ተመራጭ መዳረሻ የሚያደርጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሀዋሳ ከተማን ለእረፍት ጊዜያቸው ዘወትር እንደሚመርጧት የገለጹት ደግሞ ሰላማዊት እሸቱ ናቸው። ለዚህም የከተማዋ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ የቱሪስት መዳረሻዎች፣ እንዲሁም የሐይቅ ዳርቻ ልማቱ ከተማዋን ይበልጥ ሳቢና ማራኪ እንዳደረጋትም አስረድተዋል።
የሕዝብን የልማት ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል-አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)
Jul 5, 2026 355
ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ። በዘጠና ቀናት ዕቅድና አፈጻጸም ላይ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በደሴ ከተማ ውይይት እያካሄዱ ነው። የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የክልሉን ዕድገትና የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ አመራር በመስጠት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። በክልሉ በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። በዚህም የክረምት ሥራዎችን ጨምሮ በዋና ዋና የልማት ዘርፎች ላይ በመረባረብ፣ የተጀመረውን ዕድገትና ብልፅግና ዳር ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አክለዋል። በተለይም በየደረጃው ያለው አመራር የመረጠውን ሕዝብ በላቀ ሁኔታ ለማገልገልና ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል። ለዚህም የመንግሥትን አፈጻጸም በሁሉም ዘርፍ ማሳደግ፣የኑሮ ውድነቱን ማረጋጋት፣ የዜጎችን ገቢ ማላቅና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ማስፋፋት ላይ በማተኮር ችግሮችን የመፍታት አቅጣጫ መከተል እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል። የክልሉን ሰላም ለማጽናት በተደረገው ጥረት ውጤታማ ተግባር መከናወኑን የጠቆሙት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በቀጣይም ሰላሙን በዘላቂነት በመጠበቅ ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በመድረኩም ላይ የክልል፣የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት፤ ይበልጥ ተደራሽና ቀልጣፋ በመሆን የደንበኞችን እርካታ ያረጋግጣል
Jul 3, 2026 819
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት፤ የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ተደራሽና ቀልጣፋ በማድረግ የደንበኞችን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ የሚያረጋግጥ መሆኑን የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎችና ባለሙያዎች ገለጹ። አገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ተደራሽ እና ጥራት ያለው ለማድረግ የፌዴራል ተቋማት ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ ለማኅበረሰቡ ይበልጥ ተደራሽ በመሆን ወደ አገልግሎት የገቡት ሁለት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ ባሶች ቴክኖሎጂዎቻቸው ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት የሰጡ ናቸው፡፡ በዚህም አንደኛው ባስ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ (EV) የሚሠራ ሲሆን ሁለተኛው የተፈጥሮ ጋዝን በመጠቀም የሚንቀሳቀስና አገልግሎት የሚሰጥ ነው፡፡ እነዚህ ተንቀሳቃሽ መስኮቶች የስድስት ቁልፍ የፌዴራል ተቋማትን አገልግሎቶች የሚሰጡ ሲሆን፣ አገልግሎቶቹም ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ በመሄድ የተቀላጠፈ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው፡፡ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተጠቃሚዎች እንደገለጹት፤ ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት እጅግ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያገኟቸው ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ አቶ በኃይሉ ወርቁ በሰጡት አስተያየትም ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት ማኅበረሰቡ ባለበት ቦታ ሆኖ ፈጣንና የተቀላጠፈ የመንግሥት አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻሉን ገልጸዋል። ይህ የዲጂታል ትግበራ አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ ከሙስና የጸዳ፣ ግልጽና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑንም አክለዋል። አቶ አስቻለው ጓዴ በበኩላቸው ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት በየአካባቢው እየተዘዋወረ አገልግሎት መስጠቱ ማኅበረሰቡን ከተጨማሪ ወጪና ከተንዛዛ እንግልት እንደታደጋቸው ገልጸዋል። አሠራሩ ጊዜና ገንዘብን በአግባቡ ለመቆጠብ ያስቻለ በመሆኑም የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል፡፡ በወረፋና በተለያዩ ቦታዎች መጉላላት ሳይኖር፣ በአንድ ማዕከል በርካታ አገልግሎቶችን ማግኘት መቻሉ ጊዜንና ጉልበትን በከፍተኛ ደረጃ እየቆጠበላቸው መሆኑን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ ወርቅነሽ እሸቱ ናቸው፡፡ የአገልግሎቱ ዲጂታላይዝ መሆን ከተገልጋዩ ባሻገር ለባለሙያዎችም የላቀ የሥራ ተነሳሽነትና ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠሩን አገልግሎቱን የሚሰጡ ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡ የአገልግሎቱ ባለሙያ አቶ አሰግድ ንዋይ እንደገለጹት፣ አዲሱ አሠራር ተቋማትና ባለሙያዎች ወደ ተገልጋዩ ይበልጥ እንዲቀራረቡና ግልጽነት የሰፈነበት አገልግሎት እንዲሰጡ አስችሏል። እሌኒ ውድነህ በበኩሏ፤ አዲሱ የዲጂታል አሠራር ለሠራተኞች ጤናማ የሥራ ድባብ ከመፍጠሩም በላይ፣ የተገልጋዮች እርካታ ለባለሙያው ትልቅ መነሳሳት መሆኑን ጠቁማ፣ ተንቀሳቃሽ መሶብ ማኅበረሰቡን በእጅጉ ማስደሰቱን ገልጻለች። የፌደራል መሶብ አገልግሎት ማዕከል ምክትል ኦፕሬሽናል ዘርፍ ኃላፊ ቤዛዊት ብርሃኔ በበኩላቸው፤ ይህ ዘመናዊ አሠራር ኅብረተሰቡ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሁልጊዜም በታላቅ እምነት፣ ምቾትና አስተማማኝ በሆነ መልኩ እንዲያገኝ በር የከፈተ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል
Jul 1, 2026 1557
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻሉን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ አገልግሎቱ በተጀመረ አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ3ሺህ 600 በላይ ነዋሪዎች የዲጂታል አገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከትውልድ እስከ ሞት ያሉ ወሳኝ ኩነቶችን የሚመዘግብ ተቋም ነው፡፡ ይህንን የአገልግሎት አሰጣጡን ዲጂታላይዝ ለማድረግ ሰፊ ስራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፣ በቅርቡም አዲሱን ዲጂታል ስርዓት በስኬት አስመርቆ ስራ አስጀምሯል። ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር ነዋሪዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ወይም በኮምፒውተራቸው አማካኝነት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ምቹ አሰራር የፈጠረ ነው። በኦንላይን የተጀመሩት አራቱ ዋና ዋና አገልግሎቶችም መታወቂያን ከፋይዳ መረጃ ጋር ማስተሳሰር፣ የነዋሪነት መታወቂያ እድሳትና የጠፋን መተካት፣ ያላገባ የምስክር ወረቀት አገልግሎት እና የልደት ምስክርነት ወረቀት አገልግሎት ናቸው። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ፤አዲሱ የዲጂታል አሰራር ጊዜን በመቆጠብ፣ ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ትልቅ ጠቀሜታ እያገኙበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። ከተጠቃሚዎች መካከል የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ነዋሪ አቶ አባትዬ ተስፋዬ ፤ አገልግሎቱን በቀላሉ ከቤታቸው ሆነው በቴክኖሎጂው አማካኝነት ማጠናቀቃቸውን ገልጸው፣ የተዘጋጀላቸውን መታወቂያ ለመረከብ ብቻ ወደ ወረዳው መምጣታቸውን ተናግረዋል። ይህ አሰራር ጊዜን ከመቆጠቡ ባለፈ፣ ዘመናዊና ስልጡን አሰራር በመሆኑ ከፍተኛ እርካታ እንደፈጠረላቸውም ጨምረው አስታውቀዋል። ሌላኛው የዚሁ ወረዳ ነዋሪና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ኢሳያስ ግርማ በበኩላቸው፤ የዲጂታል አሰራሩ ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ በዘርፉ ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ አንጻር አይነተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ ሆነው በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ወይም በኮምፒውተራቸው አስፈላጊውን ሰነድ አያይዘው ካመለከቱ በኋላ የሚፈልጉት አገልግሎት በፍጥነት እየተሰጣቸው ይገኛል ያሉት ደግሞ በኤጀንሲው የኦንላይን አገልግሎት ባለሙያ የሆኑት ደሳለኝ ዘርጋ ናቸው። ተገልጋዩ ወደ ወረዳ በአካል የሚመጣው የተዘጋጀውን ሰርተፊኬት ወይም መታወቂያ ለመውሰድ ብቻ መሆኑን ባለሙያው አብራርተዋል። ሌላኛዋ የኤጀንሲው የኦንላይን አገልግሎት ባለሙያ ሶስና አወል በበኩላቸው ፤ይህ አሰራር ቀደም ሲል በወረዳዎች ላይ ይፈጠር የነበረውን ከፍተኛ የህዝብ ግርግርና የአገልግሎት አሰጣጥ ውጥረት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰው ይገኛል ብለዋል። ይህም ሰራተኞች በተረጋጋ መንፈስና በነጻነት ስራቸውን በጥራት እንዲያከናውኑ ትልቅ እገዛ ማድረጉን አክለዋል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሤ በበኩላቸው፤ አዲሱ የኦንላይን አገልግሎት አሰጣጥ በተቋሙ ይስተዋሉ የነበሩ የአገልግሎት መቆራረጦችንና የተገልጋይ እንግልትን በከፍተኛ ደረጃ እየቀረፈ መሆኑን አስታውቀዋል። አገልግሎቱ በተጀመረ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ3ሺህ 600 በላይ ነዋሪዎች ከቤታቸው ሆነው በቴክኖሎጂው መጠቀም መቻላቸውን ለአብነት አንስተዋል። የኦንላይን አገልግሎቱ በተገልጋይና በአገልግሎት ሰጪዎች መካከል ያለውን ቀጥተኛ ንክኪ በማስቀረት ብልሹ አሰራርን በጽኑ የሚከላከል መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂንና ስማርት ከተማ የመፍጠር ግብን የሚያሳካ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
የአገልግሎት እመርታ በመሶብ - የዜጎች እፎይታ እና የተሳለጠ አገልግሎት
Jul 1, 2026 1223
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2018 (ኢዜአ)፡-የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት በመቀነስ ፈጣን፣ ጥራት ያለውና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ወደ ሥራ የገባው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የዜጎችን እንግልት በመቀነስና የመንግሥት አሰራርን በማዘመን ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ነው። ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አሰራርን በአንድ ቦታ ላይ በማቅረብ፣ ዜጎች የሚፈልጓቸውን አገልግሎቶች ያለምንም ውጣ ውረድ ፈጣን፣ ጥራት ያለውና ምቹ በሆነ ሁኔታ እንዲያገኙ አድርጓል። ይህም የመንግሥትን አገልግሎት አሰጣጥ ከማሳለጡ ባለፈ፣ አጠቃላይ አሰራሩን ግልጽ በማድረግ ብልሹ አሰራርን በከፍተኛ ሁኔታ መከላከል ችሏል፡፡ የማዕከሉን አገልግሎት በተመለከተ ለኢዜአ አስተያየት የሰጡት የመዲናዋ ነዋሪ አቶ ደስታ ወዳጄነህ፣ የዲጂታል መሶብ አገልግሎት መዘርጋቱ ውድ ጊዜን የሚቆጥብና ኢትዮጵያ ወደ ላቀ የአገልግሎት ምዕራፍ እየገባች መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል። አሰራሩ ዜጎች በቀላሉ አገልግሎት እንዲያገኙ በማስቻል ጊዜያቸውን በአግባቡ ለመጠቀም እንደረዳቸውና ቀደም ሲል ትልቅ ፈተና የነበረውን እንግልት ያስቀረ አሠራር መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ሌላኛው ነዋሪ አቶ ዮሴፍ ታመነ በበኩላቸው፣ ቀደም ሲል መታወቂያ ለማውጣት ብዙ መመላለስና አድካሚ ውጣ ውረዶች የነበሩ መሆኑን አስታውሰው፣ አሁን ግን በአዲሱ አሰራር ፈጣን አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ረጅም ጊዜ ይወስድ የነበረው አገልግሎት በአሁኑ ወቅት በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ እንዲጠናቀቅ መደረጉ ነዋሪዎች በእለት ተእለት እንቅስቃሴያቸው ጊዜያቸውን እንዲቆጥቡና በቅልጥፍና እንዲስተናገዱ እንዳገዛቸው ጠቁመዋል፡፡ ይህም በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ውስጥ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችንና ተያያዥ ቅሬታዎችን ሙሉ በሙሉ ያስቀረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ይርጋለም ተሾመ በበኩላቸው፣ የዲጂታል መሶብ አገልግሎት አሰጣጥ እጅግ የተራቀቀና ቅልጥፍና የተሞላበት በመሆኑ ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ መነሻ የሚሆን ነው ብለዋል። ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር በአጠቃላይ በሀገሪቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠውና ለቀጣዩ ትውልድ መልካም አሻራ የሚጥል መሆኑንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አስቻለው አድማሱ፣ የመሶብ አገልግሎት ቀደም ሲል በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበሩ በርካታና ውስብስብ ችግሮችን ያስወገደ መሆኑን ተናግረዋል። ይህ ዘመናዊ የዲጂታል አሰራር በግለሰብ ደረጃ ምቾትን ከመፍጠሩ ባለፈ፣ እንደ ሀገርም ትልቅ እድገትና እምርታ መሆኑን በተጨባጭ ማረጋገጡን አስረድተዋል። አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል መሰጠታቸው አላስፈላጊ መጉላላቶችን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቀንስ የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ነዋሪ አቶ ብርሃን አብርሃ ናቸው። አቶ ብርሃን ከዚህ ቀደም የነበረው አሰራር እጅግ አድካሚና ውጣ ውረድ የበዛበት እንደነበር አስታውሰው፣ የአሁኑ ግን የተቀላጠፈና ምቹ መሆኑን መስክረዋል።
የኢጋድ የሳይበር የተግባር ልምምድ የአባል ሀገራትን የጋራ ደህንነት ለማረጋገጥና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል ፈጥሯል
Jun 30, 2026 1526
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የኢጋድ የሳይበር የተግባር ልምምድ የአባል ሀገራትን የጋራ ደህንነት ለማረጋገጥና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል እንደፈጠረላቸው አስተያየታቸውን የሰጡ የስልጠናው ተሳታፊ ሀገራት ተወካዮች ገለጹ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሣ) ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኢጋድ ቀጣናዊ የሳይበር የተግባር ልምምድ ሥልጠና ላለፋት አምስት ቀናት በአዲስ አበባ ተሰጥቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያን ጨምሮ ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ እና የጅቡቲ ተወካዮች ተሳትፈዋል። በጅቡቲ የሚገኘው የኢጋድ ዋና መሥሪያ ቤት የሳይበር ደህንነት እና የዳታ አስተዳደር ከፍተኛ ባለሙያ ኸድራ አሊ ዩሱፍ እንደገለጹት፤ ሥልጠናው ከፖሊሲ ቀረጻ ጀምሮ እስከ ቴክኒካዊ ልምምድ ድረስ ያሉ በርካታ ዘርፎችን ያካተተ ነበር ብለዋል። በተለይም የሳይበር ደህንነት ሥጋት መረጃ ትንተና እና የማልዌር ወይም የጎጂ ሶፍትዌሮች ምርመራ ላይ ሰፊ ትኩረት መደረጉን አመልክተዋል። የሳይበር ሥጋቶችና ጥቃቶች በተፈጥሮ ድንበር ተሻጋሪ በመሆናቸው መርሃ ግብሩ በአባል አገራቱ መካከል ያለውን የጋራ የመከላከል አቅም እና ቀጣናዊ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። በኡጋንዳ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ውስጥ ዋና የሲስተምስ አድሚኒስትሬተር ሮበርት ልዋሳ እንደተናገሩት፤ መርሃ ግብሩ እንደ ኢትዮጵያና ዩጋንዳ ያሉ የኢጋድ አባል አገራት የሳይበር ደኅንነትን እንዴት እየተገበሩት እንደሆነና ያላቸውን የአስተዳደር መዋቅር እርስ በእርስ ለመለዋወጥ ትልቅ ዕድል የፈጠረ ነው ብለዋል። የሳይበር ጥቃት ድንበር ተሻጋሪና ዓለም አቀፋዊ ሥጋት መሆኑን በመጥቀስ ጥቃቶቹን ለመቋቋም ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታና አብሮ መስራት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በደቡብ ሱዳን የብሔራዊ የሳይበር ደህንነት ቁጥጥር ማዕከል አናሊስት ዮም ማሉአል ማጆክ በበኩላቸው፤ ሥልጠናው ሙሉ በሙሉ በተግባር እና በእውነተኛው ዓለም ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የሳይበር ጥቃቶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በየአገራቱ የሚገኙ የመንግሥት መሠረተ ልማቶችን፣ የፋይናንስ ሥርዓቶችን እና የግል ተቋማትን ከጥቃት ለመጠበቅ የትኞቹ ሰርቨሮችና ሥርዓቶች ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ትልቅ ግንዛቤ ያገኘንበት ነው ብላለች። ወደ አገራቸው ሲመለሱም ይህንን ተግባራዊ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። የሶማሊያ ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኮምፒውተርና መረጃ ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን መሐመድ በበኩላቸው ሥልጠናው እጅግ አስደናቂና ከፍተኛ እውቀት የተገኘበት መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ በሳይበር ደኅንነት ዘርፍ ያላትን ልምድና ያሳየችውን ዕድገት ማጋራቷ ለአባል አገራቱ ጠቃሚ መሆኑን ጠቁመዋል። ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ከመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎችም ሰፊ እውቀትና ልምድ ማግኘታቸውን በመግለጽ ተሳታፊዎቹ በሥልጠናው መደሰታቸውን አክለዋል።
ስፖርት
ሲዳማ ቡና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ተረከበ
Jul 5, 2026 144
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦ በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ሀብታሙ በ70ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ጎሉን አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ54 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና በ68 ነጥብ ዓመቱን ጨርሷል። ጨዋታውን ተከትሎ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉ አሸናፊ የሆነው ሲዳማ ቡና ዋንጫውን ተረክቧል። የሊጉ ዋንጫ ሲዳማ ቡና በ1999 ዓ.ም ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ያሳካው ትልቁ ድሉ ነው። ሻምፒዮንነቱን ተከትሎ በቀጣዩ ዓመት ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣዩ ዓመት በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ይሳተፋል። ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ዋንጫውን ለማንሳት ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ይፋለማል። በዋንጫ ስነ ስርዓቱ ላይ በርካታ የሲዳማ ቡና ደጋፊዎች ታድመዋል። በተጨማሪም ሲዳማ ቡና ዛሬ የተጠናቀቀውን ከ20 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በማጠቃለያ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻን በመለያ ምት በመርታት ዋንጫውን አንስቷል። በዚህም ድርብ ድል አሳክቷል። በሊጉ የመዝጊያ ስነ ስርዓት የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የፕሪሚየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው የዘንድሮው የሊጉ ውድድር ዛሬ በ38ኛ ሳምንት ተቋጭቷል። ምድረ ገነት ሽሬ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ መቀሌ 70 እንደርታና አርባምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረዱ ክለቦች ናቸው። ከከፍተኛ ሊግ ያደጉት ሃላባ ከተማ እና ጋሞ ጨንቻ በቀጣዩ የውድድር ዓመት በሊጉ ይሳተፋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ ናትናኤል ዳንኤል እና የፋሲል ከነማው ታምራት እያሱ በተመሳሳይ 15 ጎሎች በጋራ የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን አጠናቀዋል። የሲዳማ ቡናው አቤል ያለው በ14 ግቦች ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል።
ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና የዋንጫ ሽልማቱን በሚረከብበት ዕለት ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ይጫወታል
Jul 5, 2026 268
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጠናቀቃል። ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና በ68 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ51 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ሲዳማ ቡና የሊጉን ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ማንሳቱን ያረጋገጠው በ36ኛ ሳምንት ከነገሌ አርሲ ጋር አንድ አቻ መለያይቱን ተከትሎ ነው። በ1999 ዓ.ም የተመሰረተው ሲዳማ ቡና የፕሪሚየር ሊጉ ዋንጫ ባለቤት መሆኑ በ19 ዓመት የክለቡ ጉዞ ውስጥ ትልቁ የሚባለው ስኬቱ ነው። ለረጅም ሳምንታት የሊጉ አናት ላይ የቆየው እና በአንጻራዊነት ወጥ አቋም ያሳየው ሲዳማ ቡና ከዛሬው ጨዋታ በኋላ ታሪካዊውን ዋንጫ የሚረከብ ይሆናል። የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ የዋንጫ አቀባበል ድባቡን ይበልጥ ለቡድኑ ያደምቀዋል። ቡድኑ ሻምፒዮን መሆኑን ተከትሎም በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ኢትዮጵያን ወክሎ በቀጣዩ ዓመት ይሳተፋል። በተጨማሪም ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር የሚፋለም ይሆናል። ዓመቱን በሁለት ዋንጫ የማጠናቀቅ እድል አለው። በ37ኛ ሳምንት ከሃዋሳ ከተማ ጋር አንድ አቻ የተለያየው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ዓመቱን በድል ለመደምደም ከሻምፒዮኑ ጋር ይፋለማል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካሸነፈ አምስተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቅቃል። ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው። ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ፍጻሜውን ያገኛል። በዝናብ ስጋት ምክንያት ከአዲስ አበባ ወደ ሃዋሳ የተዛወረው የሲዳማ ቡና እና የኢትዮ ኤሌክትሪክ የ2018 ዓ.ም የሊጉ መዝጊያ ጨዋታ እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር በሳምንቱ አጋማሽ ማስታወቁ ይታወሳል።
ብራዚል ከኖርዌይ፣ ሜክሲኮ ከእንግሊዝ ወደ ሩብ ፍጻሜ ለመግባት የሚደረጉ ተጠባቂ ፍልሚያዎች
Jul 5, 2026 266
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/ 2018 (ኢዜአ):- በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሁለት የ16 ውስጥ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ። ምሽት አምስት ሰዓት ላይ ብራዚል ከኖርዌይ በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም ይጫወታሉ። የአምስት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ብራዚል 32 ውስጥ ጃፓንን 2 ለ 1 በመርታት ቀጣዩን ዙር ተቀላቅላለች። ኖርዌይ ኮትዲቯርን 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ 16 ውስጥ ገብታለች። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ፈረንሳይ እ.አ.አ በ1998 ባዘጋጀችው 16ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በምድብ አንድ ተገናኝተው ኖርዌይ 2 ለ 1 አሸንፋለች። ቶሬ አንድሬ ፍሎ እና ኬቲል ሬክዳል በወቅቱ ለኖርዌይ ግቦቹን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው። ቤቤቶ የብራዚልን ብቸኛ ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ሀገራቱ ከ28 ዓመታት በኋላ በጥሎ ማለፍ መድረክ ተገናኝተዋል። በአጠቃላይ ብሔራዊ ቡድኖቹ እርስ በእርሳቸው ባደረጓቸው አራት ጨዋታዎች ኖርዌይ ሁለት ጊዜ ድል ሲቀናት በቀሪዎቹ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። ብራዚል ኖርዌይን እስከ አሁን አሸንፋ አታውቅም። አምስት ግቦች በዓለም ዋንጫው ያስቆጠረው የኖርዌው አርሊን ሃላንድ እና አራት ግቦች ያለው ቪኒሸስ ጁኒየር በጨዋታው የሚጠበቁ ተጫዋቾች ናቸው። የሁለቱ ቡድኖች የፊት መስመር አቅም የጨዋታውን ውጤት ይወስነዋል ተብሎ ይጠበቃል። የጨዋታው አሸናፊ ከሜክሲኮ እና እንግሊዝ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። በሌላኛው መርሐ ግብር ሜክሲኮ ከእንግሊዝ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በሜክሲኮ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ከዓለም ዋንጫው አስተናጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሜክሲኮ በ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ኢኳዶርን 2 ለ 0 በመርታት 16 ውስጥ ገብታለች። ተጋጣሚዋ እንግሊዝ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን 2 ለ 1 በመርታት ወደ ሁለተኛው የጥሎ ማለፍ ምዕራፍ ተሸጋግራለች። ሁለቱ ሀገራት በዓለም ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። እንግሊዝ እ.አ.አ በ1966 ባዘጋጀችው ስምንተኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ በምድብ አንድ ተገናኝተው አዘጋጇ ሀገር 2 ለ 0 አሸንፋለች። ሰር ቦቢ ቻርልተን እና ሮጀር ሀንት ግቦቹን ለሶስቱ አናብስቶች በወቅቱ አስቆጥረዋል። እንግሊዝ እስከ መጨረሻው በመጓዝ ብቸኛውን የዓለም ዋንጫ ክብሯን ተቀዳጅታለች። ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ከስድስት እስርት ዓመታት በኋላ ዳግም በዓለም ዋንጫው ተገናኝተዋል። በዓለም ዋንጫው አምስት ጎሎች ያስቆጠረው የእንግሊዙ ሃሪ ኬን እና ሶስት ግቦች ያለው የሜክሲኮው ጁሊያን ኪኖኔስ በጨዋታው ላይ ልዩነት ይፈጥራሉ ተብለው የሚጠበቁ ተጫዋቾች ናቸው። የዛሬ ጨዋታ አሸናፊዎች በሩብ ፍጻሜው ይገናኛሉ።
የኢትዮጵያ አትሌቶች በዓለም አቀፍ መድረኮች ድል ማስመዝገብ ቀጥለዋል
Jul 5, 2026 200
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦ በ2026 የፕሪፎንቴይን ክላሲክ -ዩጂን ዳይመንድ ሊግ እና በአሜሪካው የፒችትሪ የጎዳና ሩጫ ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊ ሆነዋል። በአሜሪካዋ ዩጂን በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር፣ በሴቶች የሁለት ማይል ርቀት ብርቱ ፉክክር የተስተዋለበት ነበር። ውድድሩን በአሸናፊነት ያጠናቀቀችው አትሌት አለሺኝ ባወቀ ስትሆን፣ የወቅቱ ፈጣን የሆነ ሰዓት 9:20.02 በማስመዝገብ በአንደኝነት አጠናቃለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሒሩት መሸሻ በ9:20.20 በሆነ ሰዓት በቅርብ ልዩነት ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በዚሁ የሁለት ማይል ውድድር ላይ የተሳተፉት ሌሎች ኢትዮጵያውያን አትሌቶችም ጠንካራ ፉክክር አድርገዋል። አትሌት ማርታ አለማየሁ በ9:21.42 4ኛ ፣አትሌት የኔዋ ንብረት በ9:22.93 7ኛ እና አትሌት አሳየች አይቼው በ9:23.04 8ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በሴቶች የአንድ ማይል ውድድር ላይ የተሳተፉት አትሌት ሳሮን በርሀ በ4:22.50 11ኛ ደረጃን እንዲሁም አትሌት ወርቅነሽ መሰለ በ4:36.80 13ኛ ደረጃን ይዘው ፈፅመዋል። በሌላ በኩል 250ውን የአሜሪካ የነፃነት ቀን በዓል በማስመልከት በተካሄደው 57ኛው የፒችትሪ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ ውድድር አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ በመጨረሻዎቹ ሜትሮች ላይ በአስደናቂ ሁኔታ ፍጥነት በመጨመር ውድድሩን በ31:02 በሆነ ሰዓት በአሸናፊነት አጠናቃለች። ሌላኛዋ አትሌት መልክናት ውዱ በ31:03 በአንድ ሴኮንድ ተቀድማ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ማጠናቀቋን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል።
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአካባቢ ጥበቃና ለስነ-ምህዳር መታደስ የላቀ አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው
Jul 5, 2026 449
አዲስ አበባ፤ሰኔ 28/ 2018 (ኢዜአ):-የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሀገሪቱን የደን ሽፋን በማሳደግ ለአካባቢ ጥበቃና ለስነ-ምህዳር መታደስ የላቀ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቋቋም፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተተገበረ ይገኛል፡፡ በዚህም ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ እስከ አሁን ባሉት ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ የደን፣ የፍራፍሬና የጥላ ችግኞችን ማልማት ተችሏል፡፡ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ ተይዞ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡ በዛሬው ዕለትም የአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ በረጲ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካሒዷል፡፡ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር አካባቢን ከብክለትና መራቆት የምንጠብቅበት አንዱ መንገድ ነው ብለዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት የተተገበረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሀገሪቱን የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን ገልጸዋል፡፡ ይህም ለዓለም የአየር ንብረት መጠበቅ በረከት እየሆነ መምጣቱን ተናግረው፤ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ረገድም ሚና እያበረከተ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ የሀገሪቱን የደን ሽፋን በማሳደግ ለአካባቢ ጥበቃና ለስነ-ምህዳር መታደስ የላቀ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በበኩላቸው፤ በረጲ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ አካባቢ በአሁኑ ወቅት በተሰራ የመልሶ ልማት ስራ ከአደጋ ስጋት ወደ ሀብትነት እየተቀየረ መጥቷል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ገዛኸኝ ዴሲሳ በበኩላቸው፤ የረጲ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ በአሁኑ ወቅት በችግኝ እየተሸፈነ ይገኛል ብለዋል፡፡ በዚህም በአሁኑ ወቅት በመልሶ መጠቀም ወደ ሀብትነት እየተቀየረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች፤ አረንጓዴ አሻራ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በየዓመቱ በንቃት እየተሳተፉ መሆናቸውን ገልጸው፤ ቀደም ሲል በአካባቢያቸው የነበሩ የቆሻሻ መጣያ መሬቶች አሁን ላይ መልሰው በማገገም በአረንጓዴ ተክሎች መሸፈናቸውን ተናግረዋል።
የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ልዑካን በታሪካዊቷ ላሊበላ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዱ
Jul 4, 2026 431
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ልዑካን ቡድን አባላት በታሪካዊቷ ላሊበላ ከተማ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች፣ በዩኔስኮ በተመዘገበው የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ቅጥር ግቢ ነው የአረንጓዴ ዐሻራቸውን ያኖሩት። በታሪካዊቷ የላሊበላ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኘው የዲፕሎማቲክ ልዑክ፣ ትናንት የዓለም ድንቅ ቅርስ የሆነውን የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በተጓዳኝም በዛሬው ዕለት በቅርስ መዳረሻው የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ቅጥር ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሂደዋል። የልዑካኑ የችግኝ ተከላ የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከቅርስና አካባቢ ጥበቃ ጋር በአርዓያነት ተሰናስሎ የሚሰራበት መሆኑን ዓለም አቀፋዊ የልማት አጀንዳ መሆኑ ተገልጿል። ጉብኝቱና የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያን ጥንታዊነት፣ አስደናቂ የኪነ-ሕንጻ ጥበብና የባህል ዕሴቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይበልጥ ለማስተዋወቅ ትልቅ አጋጣሚን ፈጥሯል። ጉብኝቱም ኢትዮጵያ ለቱሪስቶች አስተማማኝና ማራኪ መዳረሻ መሆኗን ለዓለም በመገለጥ የቱሪዝም ዘርፍ ለማነቃቃት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል። የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ተወካዮች በቅርስ ስፍራው ችግኝ መትከላቸው፣ የዓለም ቅርሶችን የመንከባከብና የአየር ንብረት ለውጥን በጋራ የመከላከል ዓለም አቀፋዊ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። የዲፕሎማቶች ጉብኝትና የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ፀጋዎችን በመጠቀም ለመልካም ገጽታ ግንባታና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ለምታደርገው ጥረት አጋዥ ሚና ይኖረዋል።
ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ስትራቴጂካዊ ፕሮግራሞችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበች ነው -ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር)
Jul 4, 2026 1164
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ስትራቴጂያዊ ፖሊሲዎችንና ፕሮግራሞችን በውጤታማነት በመተግበር ተጨባጭ ውጤት እያመጣች መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፅም አሰፋ (ዶ/ር) ገለፁ። ለመጪው ትውልድ ጽዱ፣ ጤናማና አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ የተጀመረው የ"ጽዱ ኢትዮጵያን ለትውልድ" ሦስተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደተናገሩት ሦስተኛው ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ባለፉት ሁለት ዙሮች የተገኙ ውጤቶችን በማስፋት ለሀገሪቱ ዘላቂ ልማትና አካባቢ ጥበቃ ወሳኝ አቅም የሚፈጥር ነው። ንቅናቄው ለዜጎች ጤናማና ንጹህ አካባቢ ለመፍጠር እና ለመጪው ትውልድ ፅዱ ኢትዮጵያን ለማውረስ የጋራ ቁርጠኝነትን ማረጋገጫ ነው ብለዋል። የከተሞች መስፋፋት፣ የፕላስቲክ ቆሻሻ መጨመር፣ የአደገኛ ኬሚካሎችና ቆሻሻዎች ተገቢ አያያዝ እጥረት፣ የድምፅ ብክለት እና ሌሎች የአካባቢ ችግሮች የዜጎችን ጤና፣ የአካባቢን ደህንነትና የዘላቂ ልማት ጉዞአችንን እየተፈታተኑ እንደሚገኙም አብራርተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ በርካታ ስትራቴጂያዊ ፖሊሲዎችንና ፕሮግራሞችን እየተገበረ ይገኛል ብለዋል። የአስር ዓመት የልማት ዕቅድ፣ የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ፣ የንፁህ ኃይል ሽግግር፣ የከተማ ኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች፣ አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ከረጢቶችን የሚከለክል ሕግ፣ እንዲሁም የነዳጅ ተሽከርካሪዎችን ከውጭ የማስገባት ክልከላ የዚህ ቁርጠኝነት ተጨባጭ ማሳያዎች መሆናቸውን አብራርተዋል። በመርሃ ግብሮቹ ትግበራም ተጨባጭ ውጤት መምጣቱን አንስተዋል። ሀገሪቱ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ለውጥ ችግሮች እየወሰደቻቸው ያሉ የመፍትሔ እርምጃዎችና ያላት ቁርጠኝነት በዓለም አቀፍና በአህጉር ደረጃ ያላትን ተሰሚነት ከፍ ያደረገ መሆኑንም ገልፀዋል። በተለይ የአየር ንብረት ለውጥን በዘላቂነት ለመከላከል እንደሀገር በየዓመቱ እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ከፍተኛ ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል። በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን መሪነት እየተተገበረ የሚገኘው የፅዱ ኢትዮጵያ ሀገራዊ ንቅናቄ ንፁህና ጤናማ አካባቢ ለመፍጠር እየተከናወኑ ካሉ ዓበይት ተግባራት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። የአካባቢ ጥበቃ ተቋማዊ ሥራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግም የተለያዩ ህግጋት ወደ ተግባር መግባታቸውን ተናግረዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ(ዶ/ር)፥ ባለፉት ሁለት ዙሮች የተካሄዱ የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄዎች ለአካባቢ ጥበቃ ውጤታማ ተግባራት የተከናወነባቸው መሆናቸውን ተናግረዋል። በመጀመሪያው ዙር ከ15 ሚሊየን በላይ በሁለተኛው ዙር ደግሞ ከ54 ሚሊየን በላይ ህዝብ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ዘዴዎች ተደራሽ በማድረግ በባለቤትነት እንዲሳተፉ መደረጉን አንስተዋል። 3ኛው ዙር ንቅናቄ የፕላስቲክ ብክለት፣ የአደገኛ ኬሚካሎችንና አደገኛ ቆሻሻዎችን መከላከል እንዲሁም የድምፅ ብክለትን መከላከል ላይ ያተኮረ መሆኑን ጠቅሰዋል። የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ለአካባቢ ጥበቃ መሰረት እየጣለ መሆኑን ገልጸው፥ ለስኬታማነቱ ጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎና የጋራ ቁርጠኝነትን እንደሚጠይቅ አስረድተዋል።
የአካባቢ ብክለትን መከላከል ከሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ጋር የተሳሰረ ብሔራዊ የልማትና ደኅንነት ጉዳይ ነው
Jul 4, 2026 1117
የአካባቢ ብክለትን መከላከል ከሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ጋር የተሳሰረ ብሔራዊ የልማትና ደኅንነት ጉዳይ ነው አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የአካባቢ ብክለትን መከላከልና የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ከኢኮኖሚ ምርታማነትና ከሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ጋር የተሳሰሩ ብሔራዊ የልማትና ደኅንነት ጉዳዮች መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ። ኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃና በአረንጓዴ ልማት ለአፍሪካ ተምሳሌት ሀገር መሆን መቻሏንም ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 3ኛውን ዙር የ"ጽዱ ኢትዮጵያን ለትውልድ" ሀገር አቀፍ ንቅናቄ በይፋ አስጀምረዋል። በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክትም፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት በመላ ሀገሪቱ በመደመር መንግሥት እየተተገበረ ያለው የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ልማት ከተሞችን ጽዱ፣ አረንጓዴ፣ ውብ እንዲሁም ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረጉም ባሻገር፣ የቱሪስት መስሕብነታቸውን እያሳደገው መሆኑን ተናግረዋል። ሦስተኛው ዙር የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄም ከእነዚህ ሀገራዊ መርሃ ግብሮች ጋር በተቀናጀ መልኩ እንደሚተገበር ገልጸዋል። የፕላስቲክ ብክለት፣ የአደገኛ ቆሻሻዎች አያያዝ እና የድምፅ ብክለት ለአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ብቻ ሳይሆኑ ከሕዝብ ጤና፣ ከኢኮኖሚ ምርታማነት፣ ከኢንቨስትመንትና ከሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ጋር የተሳሰሩ ብሔራዊ የልማትና ደኅንነት ጉዳዮች መሆናቸውን አስገንዝበዋል። እነዚህን ተግዳሮቶች መፍታት የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገራችንን ዘላቂ ልማት፣ ተወዳዳሪነት እና የትውልዶችን የወደፊት ዕድል የሚወስን ሀገራዊ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነውም ብለዋል። ባለፉት ሁለት ዙሮች የተካሄዱት የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄዎች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የተሳተፉባቸውና ትልልቅ ስኬቶች የተመዘገቡባቸው መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ሦስተኛው ዙር ንቅናቄም የቀደሙትን ጠንካራ ጎኖች በማጠናከር እንዲሁም የክትትል፣ የሪፖርት ሥርዓት እና የተቋማዊ ቅንጅት ክፍተቶችን በጥልቀት በመገምገም መዘጋጀቱን አስረድተዋል። ንቅናቄው በግንዛቤ ፈጠራ ላይ ብቻ ሳይወሰን በሚለኩ ውጤቶች፣ በጠንካራ ክትትልና ግምገማ እንዲሁም በተቋማዊ ተጠያቂነት ላይ በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቀዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በብክለት መከላከል፣ በአካባቢ ጥበቃና ተያያዥነት ባላቸው ሕጎች ዝርጋታና ተፈጻሚነት እንዲሁም በኅብረተሰብ ግንዛቤ ፈጠራ ላይ ተምሳሌታዊ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። የንቅናቄውን ስኬታማነት ለማረጋገጥ ሁሉም የክልል መንግሥታትና የከተማ አስተዳደሮች እንደየአካባቢያቸው ሁኔታ ግልጽ የትግበራ ዕቅድ በማዘጋጀት፣ በጀት በመመደብና ጠንካራ የክትትልና ሪፖርት ሥርዓት በመዘርጋት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል። በተለይም የክልል ፕሬዚዳንቶች፣ ከንቲባዎችና የአካባቢ ጥበቃ ተቋማት አመራሮች የመሪነት ኃላፊነታቸውን በብቃት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ለሀገራዊ ንቅናቄው መሳካት የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማኅበራት፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ሴቶችና ወጣቶች በአንድነት እንዲንቀሳቀሱም ጠይቀዋል። መጪው ትውልድ የሚረከባት ኢትዮጵያ ከሙስና፣ ከአድልዎና ከብልሹ አሠራር ብሎም ከአካባቢ ብክለት የጸዳች እንድትሆን የጋራ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። የተጀመረው ጉዞ ለጽዱ አካባቢ፣ ለጤናማ ማኅበረሰብ፣ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ እና ለተሻለች ኢትዮጵያ የሚደረግ የጋራ ጉዞ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለመጪው ትውልድ የምናስተላልፈው ትልቁ ቅርስ ጽዱ፣ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ዘላቂ ኢትዮጵያ መሆን አለበት ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 16381
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 10909
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 9714
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 9613
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jul 5, 2026 249
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 28/2018(ኢዜአ):- የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? ኢትዮጵያ እያከናወነች ነው የገጠር ትራንስፎርሜሽን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት የተጀመረው የከተሞች ኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩም ተስፋፍቶ የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗርና አመጋገብ እንዲሁም ጤናን መሰረት በማድረግ የገጠር ኮሪደር ልማት በመከናወን ላይ ይገኛል። ለጤናም ይሁን ለኑሮ ምቹ ባልሆነ ሁኔታ ለዘመናት በተመሳሳይ ሁኔታ የኖረው አርሶና አርብቶ አደሩ አሁን ላይ መሰረታዊ የአኗኗር ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በገጠር የኮሪደር ልማት የሰዎችና እንስሳት መኖሪያ እየተለየ፤ በባዮ ጋዝ እና በፀሃይ ብርሃን በሚሰራ የሃይል ምንጭ መብራት ማግኘትና ምግብ መስራት የተቻለበት፤ በጓሮ የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬዎችን መመገብ የሚቻልበት ዘመናዊ አኗኗር ጀምረዋል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን የልማት እንቅስቃሴው በጅምር ላይ ቢሆንም በብዙ አካባቢዎች እየተስፋፋ ሞደል መንደሮች እየተበራከቱ መጥተዋል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ሀማሳ በ79 ነጥብ 4 ሄክታር መሬት ላይ የተሰራው ሞዴል መንደር የዚሁ ጥረት ማሳያ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቆ ለነዋሪዎች የተላለፈው የሀማሳ ሞዴል መንደር በአንድ ግቢ ውስጥ የንጽህና መጠበቂያ፣ የተደራጀ የቤት እንስሳት ማቆያ፣ በባዮ ጋዝ የሚሰራ የሃይል አቅርቦትን እንዲሁም የተሟላ የጓሮ ግብርናን ማእከል አድርጎ የተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም መንግሥት በተለያዩ የገጠር አካባቢዎች ሞዴል ቤቶችን መስራቱን አስታውሰው ከዚህ በመነሳት ነዋሪዎቹ በራሳቸው ተነሳሽነት የራሳቸውን መኖሪያዎች መገንባት ጀምረዋል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልእክታቸው ''ንጽህና ካለ ጤና አለ፤ ምግብ ካለ ጤና አለ፤ የተስተካከለ ኮሪደር ካለ ሰላም አለ። እነዚህ ጉዳዮች ከፍተኛ ግምት ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል። የዜጎቻችንን ሕይወት ይቀይራሉ፤ የአኗኗር ዘዬአችንን ያሻሽላሉ፤ ኢትዮጵያን ወደ ምናስበው ከፍታ ወደ ምናስበው መሻሻል የመውሰድ አቅም አላቸው'' ሲሉም ተናግረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ቀጥሎ በጋሞ ዞን የ'ዮ ሆልዲንግ’ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ከጥቂት ዓመታት በፊት ለኢንዱስትሪ ግብአት የሚሆን የድንጋይ ከሰል ከውጭ ሀገር ለማስገባት እስከ 300 ሚሊዮን ዶላር ውጪ የሚደረግ መሆኑን አንስተዋል። አሁን ላይ በኢትዮጵያ የተለያዩ የከሰል ማምረቻ ፋብሪካዎች ተመርቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውንና ይህም የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ ለውጭ ገበያ የማቅረብ እድል ይፈጥራል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአርባምንጭ ዘመናዊ የኮንፈረንስ ሪዞርት መርቀው ስራ ያስጀመሩ ሲሆን በዶርዜ ሎጅ እና አካባቢው መሰረተ ልማቶችን እንዲሁም የአርባ ምንጭ ከተማን የኮሪደር ልማት፤ በከተማዋ የሚገኘውን ኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓንም ጎብኝተዋል። በሁሉም ዘርፎች ኢትዮጵያ ማከናወኗን አጠናክራ ቀጥላለች፤ እድገትና ማንሰራራቷ ላይቀለበስ ጉዞውን ቀጥሏል። ከዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች አንዱ የቱሪዝም ሚኒስቴር በዚህ ሳምንት እንዳስታወቀው የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በዓለማችን ከፍተኛ ተጓዦች ከተመረጡ የዩኔስኮ ምርጥ አምስት ቅርሶች መካከል አንዱ ሆኗል። በዩሮኒውስ የዜና አውታር በተደረገ ጥናት፤ ሁሉንም የዓለም ክፍሎች ያዩ አንጋፋ ተጓዦች ካስቀመጧቸው ተወዳጅ የዩኔስኮ የዓለም ቅርሶች መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት በግንባር ቀደምትነት ተቀምጧል። በዚሁ ሳምንትም ከአርባ በላይ ሀገራት እና ከአሥር በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ዲፕሎማቶች የላሊበላ ከተማና ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። ይህ ከፍተኛ የዲፕሎማቶች ልዑክ በቆይታው ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩትን፣ የሕንጻ ጥበብ እና የኢንጂነሪንግ ጥበብ ማስተርፒስ እንዲሁም የሃይማኖትና የታሪክ ሕያው ምስክር የሆኑትን የዓለም ቅርስ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አስተማማኝ መከታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ በመከላከያና ስትራቴጂክ የደህንነት ጥናት መስክ ያሰለጠናቸውን ተመራቂዎች በዚሁ ሳምንት አስመርቋል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ሰራዊቱ የውስጥ ባንዳና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶችን ከንቱ ህልም በማምከን የሀገርን ሉዓላዊነት በአስተማማኝ መልኩ እየጠበቀ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ቀጣናዊ የትብብር መርህ ለማደናቀፍ ታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች ግንባር ፈጥረው እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያን ከባሕር ለማስወጣት የተጠቀሙበት የረጅም ዘመናት ሴራም ዛሬ ላይ “ፅምዶ” በሚል የተሰለፉ አካላት ስለመኖራቸው ተናግረዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአደረጃጀት ልዩ እና በዘመናዊ ትጥቅ ተጠናክሮ በማንኛውም ሁኔታ ለሀገሩ ክብርና ሉአላዊነት መጠበቅ አስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል። የ12ኛ ክፍል ፈተና በሳምንቱ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ስኬታማ በሆነ መልኩ ተከናውኗል። በሁሉም አካባቢዎች ተፈታኞች በበይነመረብ (ኦንላይን) እንዲሁም በወረቀት እንደየ ዝግጅቱና ምቹ ሁኔታውን መሰረት በማድረግ ፈተናውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። በገጠር ኮሪደር አዲስ የህይወት ምእራፍ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የጊምቦ ወረዳ በተገነባው ሞዴል የገጠር መንደር የሚኖሩ አርሶ አደሮች አዲስ የህይወት ምእራፍ መጀመራቸውን ገልጸዋል። የኤሌክትሪክና ሌሎች አገልግሎቶች የተሟላለት የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር የአኗኗር ዘይቤያችንን ምቹና ዘመናዊ አድርጎታል ያሉት ነዋሪዎቹ ይህንን ላደረጉ ሁሉ እናመሰግናለን ብለዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ የተገነባውን የገጠር ሞዴል መኖሪያ መንደር መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የግብርናና ገጠር ሽግግርን እውን በማድረግ የአርሶ አደሩን አኗኗር ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ገልፀው የመብራት፣ የውሃ፣ የመንገድን ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን አርሶ አደሩ በአቅራቢያው ማግኘት የሚያስችልና የኢኮኖሚ አቅሙን የሚያሳድጉ መሆናቸውን በወቅቱ ተናግረዋል። በቀጣይም ተግባሩን በማስፋት ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግን ፍልሰት ለማስቀረት በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ በሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ አኔ ዲማ ወረዳ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰኣዳ አብዱረህማንና የከተማው ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎችም የአከባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተካሄዷል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰዓዳ አብዱረህማን በወቅቱ፤ ዛሬ የምንተክላቸው ችግኞች ለሀገራችን ብቻ ሳይሆን ለመላው ዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ የሚሰጡ ናቸው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለትውልድ ቀጣይነት አስተማማኝ ዋስትና ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)፤ በሸገር ከተማ የአካባቢውን አረንጓዴነት ለማረጋገጥና ኢኮኖሚውን ለመደገፍ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 19 ነጥብ 1 ሚሊዮን የተለያዩ ዝርያ ያላቸውና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጎ ወደ ተግባር ገብተናልም ብለዋል። የባቡር መስመር ጥገና የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በቅርቡ የጥገና ስራው የተጀመረውን የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ የባቡር መስመር ፕሮጀክት የጥገና ሂደት በዚሁ ሳምንት ጎብኝተዋል። ከአዋሽ -ኮምቦልቻ -ሃራ ገበያ 392 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን ፕሮጀክት በአራት አቅጣጫ የጥገና ሥራው እየተከናወነ መሆኑም ታውቋል። ለልማት ተነሽዎች የተገነቡ ቤቶች በዚሁ ሳምንት የጅማ ከተማ አስተዳደር ለልማት ተነሺዎች ያስገነባውን 300 መኖሪያ ቤቶች መርቆ ማስረከቡን እንመለከታለን። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ገመቹ፤ በክልሉ በገጠርም ይሁን በከተሞች ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል። የጅማ ከተማ ከንቲባ ጠሃ ቀመር፤ በከተማው በርካታ ፕሮጀክቶች በመንግስት እየተከናወኑ እንደሆኑና የተጠናቀቁትም ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በከተማዋ በዚህ አመት 80 የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ጠቅሰው ዛሬ ለልማት ተነሺዎች ተገንብተው የተላለፉ መኖሪያ ቤቶች የዚሁ ጥረት አንድ አካል ናቸው ብለዋል። እነዚህ መኖሪያ ቤቶች ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው ግንባታቸው ተጠናቆ ለ300 አባወራና እማወራዎች ተላልፈዋል ብለዋል።
ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች
Jun 29, 2026 3234
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • ምንድንነት የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም ‘አስም’ እንደሚባልም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? የኪንታሮት ህመም እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀት አለ? ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? • ምልክቶች የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ጠቁመዋል። ምልክቶቹም በአብዛኛው በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ አስገንዝበዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸዋል። ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር)፣ የእንስሳት አይነ ምድር ሽታዎች ለዚህኛው አስም አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን አስረድተዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑንም ተናግረዋል። • አጋላጭ (ለህመሙ መባባስ) መንስዔዎች አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የዓየር ብክለት፣ ጭስ)፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ዓይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? 👉ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎችዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ 👉 በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ 👉 በቀዝቃዛ የዓየር ሁኔታ ሙቀት የሚሰጡ መከላከያ ልብሶችን መልበስ፤ 👉 ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ሕጻናትን ለውስብስብ ችግር እየዳረገ ያለው የስኳር ህመም (Diabetes) እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ • ሕክምናው የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የዓየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። ከ 3 እስከ 10 በመቶ ያህሉ የዓለም ሕዝብ በአስም ተጠቂ መሆኑንም ጠቁመዋል። #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢዜአ #የጤና_ነገር
በኢትዮጵያ በገዳይነታቸው ቀዳሚ ከሆኑ አምስት በሽታዎች አንዱ -የሳምባ ምች (ኒሞኒያ)
Jun 28, 2026 2962
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ፣ የሳምባ እና የጽኑ ህሙማን ሰብስፔሻሊስት ዶክተር እስማኤል ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሳምባ ምች መንስዔዎችን፣ ምልክቶቹን፣ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎችና ሕክምናው ሳይንሳዊ ገለጻ አድርገዋል። · ምንድንነት እንደ ዶክተር እስማኤል ማብራሪያም፤ የሳምባ ምች (ኒሞኒያ) ማለት ሳምባ ላይ የሚፈጠር ኢንፌክሽ ነው። ይህም በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚከሰት ያስረዳሉ። · የሳምባ ምች ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች በምን ይለያል? ከተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎችም …) የሳምባ ምች እንደሚለይም ነው የሚገልጹት። ይህን ሲያብራሩም፤ የተለመዱት የሳምባ ህመሞች (አስም፣ ብሮንካይትስ፣ ሲኦፒዲና ሌሎች …) የሚያጠቁት የሳምባ አየር ቱቦን መሆኑን ገልጸዋል። በአንጻሩ ኒሞኒያ የሚያጠቃው፤ ካርበንዳይ ኦክሳይድ የሚወጣበትንና ኦክስጅን የሚገባበትን (ጋዝ ኤክስቸንጅ የሚካሄድበትን) የታችኛውን የሳምባ ክፍል መሆኑን አስገንዝበዋል። · መንስዔዎች እንደ ሕክምና ባለሙያው ገላጸ፤ የሳምባ ምች በርካታ መንስዔዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል በዋናነት የሳምባ ምች የሚከሰተው በቫይረስ (40 በመቶ ገደማ) እና በባክቴሪያ (እስከ 50 በመቶ ገደማ) መሆኑን ያብራራሉ። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ቢሆን በፈንገስ (ከ5 በመቶ በታች) ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች መኖሩን አንስተዋል። ባብዛኛው በቫይረስና በባክቴሪያ ምክንያት የሚከሰት የሳምባ ምች በትንፋሽ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው እንደሚተላለፍም አረጋግጠዋል ባለሙያው። · ምልክቶቹ ህመሙ ሳምባን እንደሚያጠቃ ያወሱት ባለሙያው፤ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ሳል ማሳል መሆኑን ገልጸዋል። ሳሉ ደረቅ ወይም አክታ ያለው ሊሆን እንደሚችል በመጠቆም፤ የአክታው ቀለምም ነጭ፣ ቢጫ፣ ደም የቀላቀለ ወይም የዛገ ብረት የሚመስል ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። በተጨማሪም ይላሉ፤በሁለቱም ወይም በአንዱ በኩል የደረት ውጋት እና የትንፋሽ ማጠር (ለመተንፈስ መቸገር) ከምልክቶቹ መካከል ናቸው። እንዲሁም የሳምባ ምቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ፤ ራስን መሳት፣ መረበሽ (ኮንፊውዝ መሆን ነገሮችን ወይም ሁኔታዎች ላይ የመዘባረቅ ነገር) ሊስተዋል እንደሚችል አንስተዋል። · ወደ ሕክምና ተቋም መቼ ይሂዱ? በቀላሉ የማይጠፋ ከ24 እስከ 48 ሠዓት የሚቆይ ከፍተኛ ትኩሳት ሲኖር፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት ካለ፣ ከፍተኛ የትንፋሽ ማጠር ሲስተዋል፣ ኮንፊውዝ መሆን (ነገሮችን መዘበራረቅ) ሲኖር፣ ራስን መሳት ካለ እንዲሁም እነዚህ ምልክቶች ዝቅተኛ ቢሆኑ እንኳ ተጓዳኝ ህመሞች ማለትም (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ፣ የካንሰር ታካሚ (ኬሞ ቴራፒን ጨምሮ ለካንሰር ህመም መድኃኒት እየወሰዱ ከሆነ)፣ የበሽታ መከላከል ዐቅምን የሚቀንሱ መድኃኒቶች (እንደ ፕሪኒሶሎ ያሉና መሰል) የሚጠቀሙ ከሆነ ወደ ሕክምና በመሄድ ዕርዳታ ማግኘት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምክንያቱም እነዚህ ታካሚዎች ቶሎ ካልታከሙ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሳምባ ምቹ የህመም ደረጃ ከፍ እያለ በመሄድ ለሕይዎት የሚያሰጋበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ነው ብለዋል። ·ሳምባ ምችና የአየር ሁኔታ ብርድ (ቀዝቃዛ ዓየር) በራሱ የሳምባ ምች እንደማያመጣ የሚገልጹት ባለሙያው፤ በአንጻሩ የሳምባ ምች እንዲከሰት ምቹ ሁኔታዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር ወደ ውስጥ በሚስብበት ወቅት በሰውነት ውስጥ በሚገኝ የአየር ቱቦ ላይ የሚገኙት ሲሊያ የተሰኙ ስትራክቸሮች ተግባራቸውን በአግባቡ ማከናወን ይሳናቸዋል ብለዋል። የሲሊያ ዋና ተግባርም ከአየር ጋር ወደ ውስጥ የሚገቡትን ቆሻሻ፣ ባክቴሪያ፣ ቫይረስ እና ፈንገስ በመግፋት ከሰውነት እንዲወጣ ማድረግ መሆኑን በማስገንዘብ። በተጨማሪም አንድ ሰው ቀዝቃዛ አየር በሚስብበት ጊዜ የበሽታ መከላከል ሠራዊት ተግባርን እንደሚቀንሰው ነው ያስረዱት። አክለውም በሳይንስ ብርድ መመታት የሚባል ህመም እንደሌለ በመግለጽ፤ ሰዎች በቀዝቃዛ አየር ውስጥ ሲቆዩ በሽታ የመከላከል ዐቅማቸው ስለሚቀንስ ምናልባት ሳምባ ምችን ጨምሮ ለተለያዩ ህመሞች ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አብራርተዋል። · የሳምባ ህመም እና የሳምባ ምች አንድ ነው ወይስ ይለያያል? በሕክምና ቋንቋው ‘ኒሞኒያ’ የሚባለው በአማርኛ የሳምባ ምች መሆኑን በመግለጽ፤ ህመሙም ሳምባ ላይ በሚከሰት ኢንፌክሽን የሚፈጠር መሆኑን ነው ያስረዱት ዶክተር እስማኤል። በተለየ በሽታ አምጭ ተኅዋስያን ምክንያት የሚከሰተው የሳምባ ህመም ‘ቲበርክሎሲስ’ ወይም የሳምባ ቲቢ (የሳምባ ነቀርሳ) እንደሚባል በመግለጽ በቀላሉ መፈወስ ስለማይቻል መድኃኒቱም ረዘም ላለ ጊዜ (እንደሁኔታው እስከ 6 ወርና ከዚያ በላይ) እንደሚወሰድና ከሳምባ ምች ጋር የማይገናኝ መሆኑን ተናግረዋል። · የተባባሰ ጉንፋን እና የሳምባ ምች ጉንፋን በቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰት እንደመሆኑ፤ አንድ ሰው በቫይረስ ኢንፌክሽን ሲጠቃ ባክቴሪያዎች ይህን ሁኔታ ተጠቅመው ኢንፌክሽን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል የሕክምና ባለሙያው። ስለዚህ ቫይረሱ ሳምባ አካባቢ ያሉ የአየር ቱቦዎችን ስለሚያጠቃ ለባክቴሪያ መራባት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ ይላሉ። በዚህም መሠረት አንድ ሰው ጉንፋን ይዞትና እየቆየበት ሲሄድ፤ በተደራቢነት የባክቴሪያ ኒሞኒያ (የሳምባ ምች) ሊያጠቃው እንደሚችል አስረድተዋል። · ለሳምባ ምች በይበልጥ እነማን ተጋላጭ ናቸው? የሳምባ ምች ተጋላጭነት በዕድሜ ክልል ተወስኖ ሊታይ እንደሚችል ገልጸው፤ በዚህም መሠረት ከ65 ዓመት በላይ እና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው (የስኳር፣ የኤች አይ ቪ እና የካንሰር ታካሚዎች እንዲሁም በሽታ የመከላከል ዐቅም ለመቀነስ መድኃኒት የሚወስዱ) ከሌላው ሕብረተሰብ አንጻር ለሳምባ ምች ተጋላጭ ናቸው ብለዋል። · የአሳሳቢነት ሁኔታ የሳምባ ምች አሳሳቢነት ከፍተኛ መሆኑን የሕክምና ባለሙያው አሃዛዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል። ለምሳሌ በኢትዮጵያ በተለይም በገዳይነታቸው ደረጃ ከሚጠቀሱት አምስት በሽታዎች መካከል እንደሚመደብ አንስተዋል። የሳምባ ምች በአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመግለጽ፤ የጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት በኢትዮጵያ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚደርሰው የማኅበረሰብ ክፍል በሳምባ ምች ሊጠቃ ይችላል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃም ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚደርሰው የዓለም ሕዝብ በሳምባ ምች የመጠቃት ዕድል እንዳለው አመላክተዋል። የሞት ምክንያት ከመሆን አንጻርም ይላሉ ዶክተር እስማኤል፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕጻናት ሞት ውስጥ እስከ 25 በመቶ የሚሆነው ምክንያቱ የሳምባ ምች መሆኑን ይናገራሉ። በተመሳሳይ በዓለም ላይ ከ18 እስከ 20 በመቶ ያህሉ የሞት ምክንያት የሳምባ ምች ነው ይላሉ። · የሳምባ ምችን መከላከል ይቻላል? ዶክተር እስማኤል እንዳረጋገጡት፤ የሳምባ ምችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል። ዋናው መከላከያውም ክትባት መሆኑን በመግለጽ። በተለይም ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ሕጻናት የሳምባ ምች ክትባት በመከተብ ለበሽታው እንዳይጋለጡ መካለከል ይቻላል ብለዋል። ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው፣ ከ65 ዓመት በላይ የሆናቸው እንዲሁም ቋሚ የሳንባ ህመም ያለባቸው ክትባቱን በመውሰድ ኒሞኒያን መከላከል እንደሚችሉ አስረድተዋል። በተጨማሪም በምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችልን የሳምባ ምች የአመጋገብ ሥነ-ሥርዓትን በማስተካከል አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል አመላክተዋል። በትንፋሽ ስለሚተላለፍ በሳምባ ምች ከተጠቃ ሰው ጋር ንክኪ ባለማድረግ፤ ማስክ በመጠቀም፣ በተፋፈገ (በጣም በተጨናነቅ) ሁኔታ ውስጥ ባለመሆን ተስፋፊነቱን መከላከል እንደሚቻልም ጠቁመዋል። · ሕክምና የሳምባ ምች እንደሚታከም ያስገነዘቡት ዶክተር እስማኤል፤ እንደ በሽታው ደረጃ የሚወሰን ሆኖ ሕክምናው ከተመላላሽ በሆስፒታል ተኝቶ እስከ መታከም ሊደርስ እንደሚችል አስረድተዋል። በዚህም መሠረት የህመሙ ደረጃ ከፍተኛ ካልሆነ በተመላላሽ፤ ከፍተኛ ከሆነ ከ5 እስከ 7 አንዳንዴም ከዚያ በላይ ለሆኑ ቀናት እንደሚታከም አክለዋል። ምልክቶች እንደታዩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ አዋጭና ቶሎ ለመፈወስ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #የጤና_ነገር
ከተጽዕኖ ፈጣሪነትና ተደማጭነት መጎልበት እስከ የአኅጉር ድምጽ መሆን - የኢትዮጵያን ታላቅነት የገለጠው የዲፕሎማሲው ዘርፍ ስኬት
Jun 25, 2026 3644
በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረቷ የፓን አፍካኒዝም ንቅናቄን በማንሳት አኅጉራዊ ተቋማት እንዲመሠረቱ ፊታውራሪ ከመሆን ጀምሮ ለጎረቤቶቿ ሰላም ጉልኅ ሚና ተጫውታለች፤ አሁንም ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔን እያሰረጸች በርካቶች እንዲጋሯት አድርጋለች። እንደ ሀገር ከለውጡ መንግሥት ወዲህ ከተገኙ በርካታ ትላልቅ ስኬቶች መካከል በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው አንዱ ነው። ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል እየተስፋፋ ያለው የጉበት ስብን (ቅባት) እንዴት መከላከል ይቻላል? ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የለውጡ መንግሥት የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ዋነኛ መለኪያም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ነው። የኢትዮጵያ ሁኔታዎችን የማሰብ፣ የመፈለግና የመከወን ሂደት ንጥል (ለራስ ብቻ የሚል) ሳይሆን፤ በወንድማማችነት/እህትማማችነት ዕሳቤ በጋራ ማደግን ያነገበ ነው። ይህ ሂደቷም በበርካታ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ እንዲሁም አኅጉር አቀፍ ተቋማት ተወድሷል። በዚህም ሐሳቦቿ ቅቡል ሲሆኑ ተመልክተናል። ኢትዮጵያ የ#BRICS አባል መሆን መቻሏ አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ይህም ተሰሚነቷን ያረጋገጠ ማስረጃ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ተያያዥ ጉዳዮች ዘርፈ-ብዙ ጥቅም በማስገኘት የበለጸገች ኢትየጵያን ዕውን የማድረግ ጉዞው ያፋጥናል። ወዲህ ደግሞ በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልና አፍሪካን በመወከል ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና መመረጧም የአኅጉሪቱ ድምጽ መሆኗን ይነግረናል። ዓለም አቀፍ ብሎም አኅጉር አቀፍ የሆኑ በርካታ ኮንፈረንሶችም በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እንዲካሄዱ መደረጉ አንድምታው ብዙ ነው። በብቃት ማስተናገዷ ደግሞ ሌላኛው ጥንካሬዋ። ሌላው የሀገራችንን የተጨበጠ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስኬት የሚገልጽልን፤ የዓለም የዓየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን (COP32) እንድታዘጋጅ መመረጧ ነው። ይህን ትልቅ ዕድል በርካቶች ስለተመኙት አላገኙትም፤ ኢትዮጵያ ግን ዜጎቿን አስተባብራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቁርጠኛ አመራር ሰጭነት ባከናወነችው ያላሰለሰ ትጋት አግኝታዋለች። ግጭት ባለባቸው የቀጣናው ሀገራትም በመንግሥታቱ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት ሥር ከምታበረክተው ከፍተኛ አስተዋጽዖ ባለፈ፤ በግሏ የሰራችው ብዙ ነው። ከራሷ አልፋ ለጎረቤቶቿ ዘብ መሆኗ፤ በአብሮነት መኖርን እና በጋራ ማደግን በተግባር የገለጠች ሀገርም ያደርጋታል። ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ በሚለው ቅድሚያ ለሀገር በቀል ዕውቀቶች በሩን ክፍት ባደረገው ትጋቷም፤ በበርካታ የአኅጉሪቱ ሀገራት ዘንድ ምሥጋና አስችሯታል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲዋም በተለያዩ ሀገራት በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎቿን ከሀገራቱ እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመነጋገር በተሳካ ሁኔታ ልጆቿን ወደ ዕቅፏ መልሳለች፤ በቅርቡ በሳዑዲ ዓረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምኅረት ዐዋጅ እንዲሰጣቸው መደረጉ አንድ ማሳያ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፤ ኢትዮጵያ አፍሪካን ጨምሮ በተለያዩ አኅጉራት በሚገኙ ሀገራት መሪዎችና ተወካዮች ዘንድ በስፋት የተመረጠችና የተጎበኘች ሀገር መሆኗን ማስታወስ ተገቢ ነው። ከጉብኝት ባለፈ ትላልቅ ስምምነቶችም የተፈራረመች መሆኗን ልብ ማለት ይገባል፤ ይህም የምታነሳውን ሐሳብ ገዥነትና የአፍሪካ መግቢያ በር መሆኗን ያሳያል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ መሆኑን መረዳት ይገባል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድርድር ሂደት የተጎናጸፈችው የዲፕሎማሲ ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መነቃቃት መፍጠሩንም ማጤን ያስፈልጋል። ይህ የተሳካው ሀገሪቱ ኢትዮጵያ መንገዷም የጋራ ልማትን የሰነቀ ዕውነት በመሆኑ ነው። በቀጣይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለአንዲት ሀገራቸው አምባሳደር በመሆን፤ የዲፕሎማሲውን ሥራ በይበልጥ ማገዝ ይጠበቅባቸዋል። ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ካልሠሩ ማን ለሀገራቸው ሊሠራ ይችላል?
ትንታኔዎች
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 907
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 1468
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ትላንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሳሰር - የመደመር መንግስት እይታ በቱሪዝም
Jul 1, 2026 1546
በዮሐንስ ደርበው ቱሪዝም ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመላው ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ በአህጉራችን አፍሪካም ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙበት ሃገራት እንዳሉ ይታወቃል። ቱሪዝም ከገቢነት ከኢኮኖሚያዊ እቅምነት ባለፈ ትውልድን ያስተሳስራል ብሄራዊ ትርክትን ለመገንባትም ያግዛል ። ትላንትን ከዛሬ ዛሬንም ከነገ ጋር የሚያስተሳስር ነው። “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግስት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ በማድረግም ይጠበቅባቸዋል።
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 5257
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 7201
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 18940
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 11997
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 17756
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 3445
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 2732
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።