ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ባንኩ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደራሽ በማድረግ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማረጋገጥ አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል
Jun 4, 2026 179
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደራሽ በማድረግ የደንበኞቹን ፍላጎት ከማረጋገጥ አንጻር አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ (Visa) ኩባንያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን አዲስ የግብይትና የክፍያ ካርድ አገልግሎት ዛሬ ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ፤ ባንኩ በዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህም የባንኩ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሼባማይልስ (ShebaMiles) ደንበኞች በጋራ ሊጠቀሙበት የሚችሉትን የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ (CBE-ET Cobranded Visa Prepaid Card) ዛሬ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ የሼባማይልስ አባላት የኢ-ኮሜርስ ክፍያዎችን በቀላሉ መፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፥ በሚያደርጉት ግብይትም የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ በር ይከፍታል ብለዋል። ደንበኞች በካርዱ ግብይት በሚፈጽሙበት ወቅት የሼባማይልስ ነጥቦችን የሚያከማቹ ሲሆን፥ የተሰበሰቡትን ነጥቦች ለአውሮፕላን ትኬት መግዣና ለሌሎች የሼባማይልስ ማበረታቻ ጥቅማጥቅሞች ማዋል እንደሚችሉ አብራርተዋል። የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያዴቻ በበኩላቸው፤ የዚህ የቪዛ ካርድ ይፋ መሆን ለአየር መንገዱ የሼባማይልስ ደንበኞች ዘመናዊና የተቀላጠፈ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያና ሕዝቧ አሸናፊነት በተግባር የታየበት ነው
Jun 4, 2026 319
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያና ሕዝቦቿ አሸናፊነት በተግባር የታየበት መሆኑን ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት አስታወቀ። የትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የምርጫ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ምርጫው ስንሻው እንደገለጹት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያውያንን እውነተኛ ፍላጎት ያንጸባረቀና የሀገሪቷን ታሪካዊ ጠላቶች ቅስም የሰበረ ክስተት ነው። ሕዝቡ ለሀገሩ ሰላምና ሉዓላዊነት ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበት መሆኑንም አክለው ገልጸዋል። ሀገርን ከጥፋት ጠብቆና ተቻችሎ መንግሥት የሚያቆመው ራሱ ሕዝቡ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዘንድሮ ምርጫ እውነተኛው አሸናፊ ሕዝቡ መሆኑን አስገንዝበዋል። ምርጫው እንዳይሳካ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ከፍተኛ ጫናዎች ቢቃጡም፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉንም ፈተናዎች በብስለትና በጽናት ተቋቁሞ መምረጡን ገልጸዋል። ሕዝቡ ሰላም ወዳድ በመሆኑ ምርጫው በስኬትና በድል ሊጠናቀቅ መቻሉን የገለጹት ኃላፊው፤ ለዚህም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሊመሰገንና ሊደነቅ እንደሚገባው ተናግረዋል። "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" ለሀገር ዘላቂ ሰላም የሚበጀው ሰላማዊ ትግል ብቻ ነው የሚለውን መርህ በመከተል ወደ ምርጫው መግባቱን የጠቀሱት ኃላፊው፤ በዚህም ፓርቲያቸው ከሕዝቡ ጋር በመሆን ታሪካዊ አሻራውን ማኖሩን አስገንዝበዋል። የዘንድሮው ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ ታዛቢዎች ጭምር እውቅና ያገኘ መሆኑን ያመለከቱት ኃላፊው አቶ ምርጫ፤ ለአብነትም የአፍሪካ ኅብረት፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ አሜሪካ እና ጃፓንን ጨምሮ በርካታ ሀገራትና ድርጅቶች የምስክርነት ቃላቸውን የሰጡበትና ኢትዮጵያውያን መቻላቸውን ለዓለም ያሳዩበት አጋጣሚ እንደሆነ አብራርተዋል። የምርጫው ሂደት ስኬታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ-ምርጫና በምርጫ ወቅት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ያከናወናቸው ተግባራት ለውጤቱ መገኘት ቁልፍ ሚና እንደነበራቸው ገልጸዋል፡፡ ለሂደቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የጸጥታ አካላት፣ ለሲቪል ማኅበራትና በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች ፓርቲው ያለውን ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ኢትዮጵያ ከአበረታች ቅመሞች ነጻ የሆነ ስፖርት ለመገንባት የጸና አቋም አላት
Jun 4, 2026 379
አዳማ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አበረታች ቅመሞችን በመዋጋት ንጹህ ስፖርት ለመገንባት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን የኢትዮጵያ የፀረ አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መኮንን ይደርሳል ገለጹ። ባለስልጣኑ በስፖርት ውስጥ የተከለከሉ አበረታች ቅመሞች (Doping) እና ዘዴዎችን አስመልክቶ ለስፖርት ጋዜጠኞች ያዘጋጀው የስልጠናና የውይይት መድረክ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። ስልጠናው የተዘጋጀው ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር ጋር በመተባበር ነው። የመድረኩ ዋና ዓላማ፥ ዶፒንግ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመከላከል ባለስልጣኑ ለጀመረው ስራ ስኬት የስፖርት ጋዜጠኞች የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ማስቻል ነው። አቶ መኮንን ይደርሳል ባለስልጣኑ ከቁጥጥር፣ ምርመራ እና ህጋዊ እርምጃ ባለፈ ሰፊ የንቅናቄ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝና በተለይም ለስፖርተኞች ተከታታይ ስልጠናዎችን በመስጠት ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ አበረታች ቅመሞች በትምህርት ስርዓት ውስጥ መካተቱ መንግስት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይና ይህም በዘላቂነት ንጹህ ስፖርትን ለመፍጠር እየተከናወነ ላለው ስራ ወሳኝ ሚና ይጫወታል ብለዋል። የስፖርት ፌዴሬሽኖች እና የስፖርት ስልጠና ማዕከላት የስልጠና ማዕቀፎችን በማዘጋጀት ለስፖርተኞች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም አንስተዋል። ከምርመራ እና ቁጥጥር ጋር በተገናኘም የአበረታች ቅመሞች ተጋላጭነት ያለባቸው የስፖርት አይነቶችን በመለየት ተደራሽነትን ለማስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በራሷ ምርመራ ማድረግ የሚያስችል አቅም እንድትፈጥር የተጀመሩ ስራዎች በጥሩ መስመር ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው በቅርቡ የምርመራ ላቦራቶሪ ስራ ለማስጀመር እቅድ መያዙን ጠቁመዋል። አበረታች ቅመሞችን የሚጸየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር እና የንጹህ ስፖርት እሳቤ እንዲሰርጽ በማድረግ ረገድ የሚዲያው ሚና ወሳኝ መሆኑንም አመልክተዋል። የኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ንዋይ ይመር ጋዜጠኞች በአበረታች ቅመሞች ዙሪያ ስነምግባርን ባከበረ መልኩ ዘገባዎችን ማቅረብ እንዳለባቸው አመልክተዋል። ጋዜጠኞች በተከለከሉ አበረታች ቅመሞች እና በተፈጥሯዊ አቅም የሚገኙ ውጤቶች መካከል ያለውን ግልጽ ልዩነት ማወቅ እንዳለባቸውም ነው የገለጹት። አንድ ስፖርተኛ እስካልተረጋገጠ ድረስ ንጹህ የመሆን መብቱን (Presumption of Innocence) ጠብቆ መዘገብ እንዲሁም ታዳጊ ስፖርተኞች ህግና ስነ-ልቦናዊ ጥበቃ ሊደረግላቸው የሚገባ መሆኑን ከግምት ማስገባት እንደሚያስፈልግም አመልክተዋል። በአጠቃላይ ጋዜጠኞች ሙያዊ ስነምግባርን አክብሮ በተከለከሉ የአበረታች ቅመሞች መከላከልና ቁጥጥር ላይ ኃላፊነት በተሞላበትና ብሔራዊ ፍላጎት ባማከለ መልኩ ገንቢ ሚና መጫወት እንደሚገባቸው አሳስበዋል። በመድረኩ የተሳተፉ የስፖርት ጋዜጠኞች በበኩላቸው ስልጠናው ወቅቱን የጠበቀና የፀረ አበረታች ቅመሞች ስራዎች ላይ ግንዛቤ በማሳደግ ማህበረሰቡን ለማስተማር መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
በክልሉ ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ
Jun 4, 2026 330
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለፁ፡፡ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ሀዋሳን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ጎብኝተዋል፡፡ ርእሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ በክልሉ የሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በይፋ ሥራ ከጀመረ በኋላ ባሉት ዘጠኝ ወራት ከ50 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት መሰጠቱን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ተገልጋዮች በማእከሉ በተሰጣቸው አገልግሎት እርካታ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። አገልግሎቱን ወደ ሁሉም አካባቢዎች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በቅርቡ ስራ የጀመረውን የሀዋሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የክልሉ ከተሞችም አገልግሎቱን በማስፋት ህዝቡ ሳይንገላታ የተቀላጠፈ አገልግሎት በቀላሉ እንዲያገኝ ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን ገልፀው በግንባታ ላይ ያሉና በአጭር ጊዜ ውስጥ ለአገልግሎት የሚበቁ ማዕከላት መኖራቸውን አመልክተዋል፡፡ በሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመገኘት ከተገለገሉ ነዋሪዎች መካከል አቶ ወንደሰን አሸቴ፤በማዕከሉ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ወደ ማዕከሉ በመጡ በ30 ደቂቃ ውስጥ የሚፈልጉትን አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ማግኘታቸውን ገልፀዋል፡፡ በማዕከሉ የአሻራ አገልግሎት እንዳገኙ የተናገሩት አቶ ፈጠነ አድማሱ በበኩላቸው በአጭር ጊዜ የተቀላጠፈ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ ጉዳያቸውን በጊዜ ጨርሰው ወደ ሌላ የዕለት ተግባራቸው መሄድ እንደቻሉም አስረድተዋል፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ግልፅና የተቀላጠፈ አገልግሎት ማግኘት መቻሉ በራሱ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝታቸው የሲዳማና የሀዋሳ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ማዕከላትን እንዲሁም በወንዶ ገነትና ለኩ ከተሞች እየተገነቡ ያሉ ማዕከላትን የተመለከቱ ሲሆን ሌሎች የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት መፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jun 4, 2026 436
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት መፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ምሁራን ገለጹ። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ለዓለም አቀፍ ንግድ ዋነኛ መተላለፊያ፣ የኃያልነት ፍትጊያ ማዕከልና ያልተነኩ ሃብቶች ወደ አሏቸው የአፍሪካ ሀገራት ዋና መግቢያ በር ሆኖ ያገለግላል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአፍሪካ ቀንድ ዓለም አቀፍ ፍላጎትና ተግዳሮት የሚንፀባረቅበት ስትራቲጂክ ቀጣና ነው። ለአብነትም አሜሪካ፣ ቻይና፣ የአውሮፓና የመካከለኛው ምስራቅ የባሕረ ሰላጤ ሀገራት ስትራቴጂክ ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም የትኩረት ማዕከላቸው ማሰሪያ አድርገው እንደሚመለከቱት ገልጸዋል። በሌላ መልኩም የሽብር ኃይሎች ደካማ የመንግሥት መዋቅሮችንና ድንበሮችን በመጠቀም ዓለም አቀፍ ትኩረት ለመሳብና የኢኮኖሚ ምንጭ ለማግኘት መሞከራቸው የቀጣናው ሁነኛ ስጋት አድርጓቸዋል ብለዋል። ኢትዮጵያም ቅድሚያ ለጎረቤት በሚሰጠው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ በኢኮኖሚ ትስስር እንዲሁም በሰላምና ደኅንነት ዘርፍ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን አንስተዋል። ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባሻገርም የተጋመደውን የቀጣናው ህዝብ በኃይል እና በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር ለቀጣናዊና አህጉራዊ የንግድ ስምምነት ትግበራ መሪ ሚናዋን እየተወጣች እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በትራንስፖርትና በዲጂታል መሰረተ ልማት፣ በወደብና የባሕር በር አማራጭ የማስፋት ስራ ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ውጤታማ አካሄድ እየተከተለች መሆኑን አስረድተዋል። የምስራቅ አፍሪካ የሽብር ኃይሎችን ህልም በማምከን የምታበረክተው ጉልህ አስተዋጽኦም ለሁለትዮሽና ባለ ብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ውጤታማነት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ብለዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን አንድነትና ጥንካሬ ከውጤታማ ዲፕሎማሲ ጋር በማጣጣም የባሕር በር ባለቤትነትና የማሪታይም ስትራቴጂን ማረጋገጥ እንዳለባት አስረድተዋል። ለዚህም ከቀጣናው ሀገራትና ኃያላኑ ጋር ስትራቴጂክ አጋርነትን በማጎልበት የህዝብ ለህዝብ መስተጋብርና ስብጥርን በትልቅ የዲፕሎማሲ መሳሪያነት መጠቀም እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያን የጎረቤት ሀገራት የብልጽግና ዋስትናነት የሚያጎላ የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት ስትራቴጂ ቀርጾ መተግበር እንደሚገባም ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ መከላከያ ኮሌጅ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አየለ በከሪ በበኩላቸው፤ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሕዝቦች በቋንቋ፣ በሃይማኖትና በባሕል የጋራ ዕሴቶች የተጋመዱ ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብና የልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ኢኮኖሚ ውህደትን ለማፋጠን የምታደርገው ውጤታማ ጥረት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጸዋል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ቅቡልነት በማሳደግ የተፅዕኖ ፈጣሪነት አቅሟን ማጎልበት ያስቻለ ስኬት ማስገኘቱን ተናግረዋል። በቀጣይም የምስራቅ አፍሪካን የኢኮኖሚ ውህደት በማፋጠን፣ የውስጥና ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና ደኅንነትን በማስከበር ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎቷን ማረጋገጥ እንደሚኖርባት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፖለቲካ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያና ሕዝቧ አሸናፊነት በተግባር የታየበት ነው
Jun 4, 2026 319
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያና ሕዝቦቿ አሸናፊነት በተግባር የታየበት መሆኑን ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት አስታወቀ። የትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የምርጫ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ምርጫው ስንሻው እንደገለጹት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያውያንን እውነተኛ ፍላጎት ያንጸባረቀና የሀገሪቷን ታሪካዊ ጠላቶች ቅስም የሰበረ ክስተት ነው። ሕዝቡ ለሀገሩ ሰላምና ሉዓላዊነት ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበት መሆኑንም አክለው ገልጸዋል። ሀገርን ከጥፋት ጠብቆና ተቻችሎ መንግሥት የሚያቆመው ራሱ ሕዝቡ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዘንድሮ ምርጫ እውነተኛው አሸናፊ ሕዝቡ መሆኑን አስገንዝበዋል። ምርጫው እንዳይሳካ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ከፍተኛ ጫናዎች ቢቃጡም፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉንም ፈተናዎች በብስለትና በጽናት ተቋቁሞ መምረጡን ገልጸዋል። ሕዝቡ ሰላም ወዳድ በመሆኑ ምርጫው በስኬትና በድል ሊጠናቀቅ መቻሉን የገለጹት ኃላፊው፤ ለዚህም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሊመሰገንና ሊደነቅ እንደሚገባው ተናግረዋል። "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" ለሀገር ዘላቂ ሰላም የሚበጀው ሰላማዊ ትግል ብቻ ነው የሚለውን መርህ በመከተል ወደ ምርጫው መግባቱን የጠቀሱት ኃላፊው፤ በዚህም ፓርቲያቸው ከሕዝቡ ጋር በመሆን ታሪካዊ አሻራውን ማኖሩን አስገንዝበዋል። የዘንድሮው ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ ታዛቢዎች ጭምር እውቅና ያገኘ መሆኑን ያመለከቱት ኃላፊው አቶ ምርጫ፤ ለአብነትም የአፍሪካ ኅብረት፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ አሜሪካ እና ጃፓንን ጨምሮ በርካታ ሀገራትና ድርጅቶች የምስክርነት ቃላቸውን የሰጡበትና ኢትዮጵያውያን መቻላቸውን ለዓለም ያሳዩበት አጋጣሚ እንደሆነ አብራርተዋል። የምርጫው ሂደት ስኬታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ-ምርጫና በምርጫ ወቅት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ያከናወናቸው ተግባራት ለውጤቱ መገኘት ቁልፍ ሚና እንደነበራቸው ገልጸዋል፡፡ ለሂደቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የጸጥታ አካላት፣ ለሲቪል ማኅበራትና በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች ፓርቲው ያለውን ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት መፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jun 4, 2026 436
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት መፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ምሁራን ገለጹ። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ለዓለም አቀፍ ንግድ ዋነኛ መተላለፊያ፣ የኃያልነት ፍትጊያ ማዕከልና ያልተነኩ ሃብቶች ወደ አሏቸው የአፍሪካ ሀገራት ዋና መግቢያ በር ሆኖ ያገለግላል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአፍሪካ ቀንድ ዓለም አቀፍ ፍላጎትና ተግዳሮት የሚንፀባረቅበት ስትራቲጂክ ቀጣና ነው። ለአብነትም አሜሪካ፣ ቻይና፣ የአውሮፓና የመካከለኛው ምስራቅ የባሕረ ሰላጤ ሀገራት ስትራቴጂክ ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም የትኩረት ማዕከላቸው ማሰሪያ አድርገው እንደሚመለከቱት ገልጸዋል። በሌላ መልኩም የሽብር ኃይሎች ደካማ የመንግሥት መዋቅሮችንና ድንበሮችን በመጠቀም ዓለም አቀፍ ትኩረት ለመሳብና የኢኮኖሚ ምንጭ ለማግኘት መሞከራቸው የቀጣናው ሁነኛ ስጋት አድርጓቸዋል ብለዋል። ኢትዮጵያም ቅድሚያ ለጎረቤት በሚሰጠው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ በኢኮኖሚ ትስስር እንዲሁም በሰላምና ደኅንነት ዘርፍ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን አንስተዋል። ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባሻገርም የተጋመደውን የቀጣናው ህዝብ በኃይል እና በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር ለቀጣናዊና አህጉራዊ የንግድ ስምምነት ትግበራ መሪ ሚናዋን እየተወጣች እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በትራንስፖርትና በዲጂታል መሰረተ ልማት፣ በወደብና የባሕር በር አማራጭ የማስፋት ስራ ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ውጤታማ አካሄድ እየተከተለች መሆኑን አስረድተዋል። የምስራቅ አፍሪካ የሽብር ኃይሎችን ህልም በማምከን የምታበረክተው ጉልህ አስተዋጽኦም ለሁለትዮሽና ባለ ብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ውጤታማነት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ብለዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን አንድነትና ጥንካሬ ከውጤታማ ዲፕሎማሲ ጋር በማጣጣም የባሕር በር ባለቤትነትና የማሪታይም ስትራቴጂን ማረጋገጥ እንዳለባት አስረድተዋል። ለዚህም ከቀጣናው ሀገራትና ኃያላኑ ጋር ስትራቴጂክ አጋርነትን በማጎልበት የህዝብ ለህዝብ መስተጋብርና ስብጥርን በትልቅ የዲፕሎማሲ መሳሪያነት መጠቀም እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያን የጎረቤት ሀገራት የብልጽግና ዋስትናነት የሚያጎላ የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት ስትራቴጂ ቀርጾ መተግበር እንደሚገባም ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ መከላከያ ኮሌጅ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አየለ በከሪ በበኩላቸው፤ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሕዝቦች በቋንቋ፣ በሃይማኖትና በባሕል የጋራ ዕሴቶች የተጋመዱ ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብና የልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ኢኮኖሚ ውህደትን ለማፋጠን የምታደርገው ውጤታማ ጥረት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጸዋል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ቅቡልነት በማሳደግ የተፅዕኖ ፈጣሪነት አቅሟን ማጎልበት ያስቻለ ስኬት ማስገኘቱን ተናግረዋል። በቀጣይም የምስራቅ አፍሪካን የኢኮኖሚ ውህደት በማፋጠን፣ የውስጥና ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና ደኅንነትን በማስከበር ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎቷን ማረጋገጥ እንደሚኖርባት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው
Jun 4, 2026 509
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፤ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እና የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ ከአንጎላ ሪፐብሊክ፣ ከባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ እና ከኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጋር ያደረገቻቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ ሪፖርቶችና የውሳኔ ሃሳቦችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። እነዚህ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆች ለንግድና ኢንቨስትመንት፣ ለቱሪዝም፣ ለዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲሁም የአየር ትራንስፖርት መዳረሻዎችን ለማስፋፋት ያላቸውን ከፍተኛ ጠቀሜታ አብራርተዋል። በተጨማሪም ስምምነቶቹ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቁና በዘርፉ ያላትን ሚና በማጉላት ተጠቃሚነቷን የሚያሳድጉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። ምክር ቤቱም በቀረቡት ረቂቅ አዋጆች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ አዋጆቹን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። ከምክር ቤቱ አባላት በኩልም የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆቹ የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸው ተገልጿል። በሌላ በኩል፣ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመው ስምምነት ረቂቅ አዋጅም በምክር ቤቱ ጸድቋል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፤ ስምምነቱ የሀገሪቱን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን፣ ለዓሳ ሀብት ልማት፣ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ለማሳደግና በዘርፉ የግል ባለሀብቶችን ለመሳብ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማትን አቅም ለማሳደግና የምርምር ሥራዎችን ወደ ገበያ አውጥቶ ለማቅረብ ያለውን ጠቀሜታም አንስተዋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት በተፈረመው የስምምነት ረቂቅ አዋጅ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ፣ አዋጁን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫን ሰላምና ደኅንነት አፈፃፀም ገመገመ
Jun 4, 2026 463
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፀጥታና ደኅንነት አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መስሪያ ቤት ተገምግሟል። በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የጋራ ግብረ ኃይሉ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫው ወቅትና ከምርጫ በኋላ ያሉ ስራዎችን እንደ ሀገር ዕቅድ አውጥቶ በቅንጅት በመመራቱ፤ በተግባር የተፈተሸ፣ የተናበበና ሰላምን ለማፅናት ጀግንነት የታየበት ተግባር በመፈፀሙ ምርጫው በሰላም ሊጠናቀቅ ችሏል ብለዋል። ኮሚሽነር ጀነራሉ አያይዘውም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶት በፀጥታና ደህንነት ተቋማት ላይ በተሰራው ሪፎርም አሁን ላይ በተጨባጭ ትላልቅ ተልዕኮዎችን መሸከም የሚችሉ የፀጥታ ተቋማት መፈጠራቸውን በምርጫው ላይ የተመዘገበው ውጤት ማሳያ ነው ብለዋል። የጋራ ግብረ-ኃይሉ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ጠላቶች የተቀናጀውን ከፍተኛ ሴራ ያከሸፈ፣ ያመከነና የሀገርን ሉዓላዊነት ያረጋገጠ፤ የሪፎርሙ ውጤት በተግባር የተለካበትና የታየበት መሆኑንም ገልፀዋል። እንደ ፀጥታ ተቋም መኩራትና መመካት ያለብን በኢትዮጵያ ህዝብ ነው ያሉት ኮሚሽነር ጀነራል በሀገራችን ላይ እየሆነ ያለውን ተረድቶ፣ ሁሉንም በሚዛን አስቀምጦ፣ የምርጫው ቀን ሲደርስ ለሁላችንም ትምህርት ያስተላለፈ የሀገር አንድነት እና ሉአላዊነትን ያጸና የኢትዮጵያ ህዝብ ታላቅ ህዝብ መሆኑን ያረጋገጠበት እንዲሁም ከዚህ በኋላ መንግስት በካርድ እንጂ በጥይት አይሆንም የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ምርጫ መሆኑን ገልፀዋል። በቀጣይም በሽብርተኞችና በፅንፈኞች ላይ የተጀመረው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለፀው የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይሉ፤ የምርጫው ውጤት ታውቆ አዲስ የመንግስት ምስረታ እስከሚከናወን እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ያሉ ሕዝባዊና መንግስታዊ ሁነቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ የፀጥታ ሥራው ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቅጣጫ አስቀምጧል።
የምርጫ ሂደቱ እውነተኛ ዴሞክራሲ በተግባር ፀንቶ የታየበት ነው- የጋራ ምክር ቤቱ
Jun 4, 2026 529
ጋምቤላ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፡- የምርጫ ሂደቱ ቅቡልነት ያለውና እውነተኛ ዴሞክራሲ በተግባር ጸንቶ የታየበት መሆኑን በጋምቤላ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ። በክልሉ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ በማስመልከት ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢና የኢዜማ ጋምቤላ ቅርንጫፍ ምክትል መሪ ኮማንደር ጋትቤል ቦል፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። የክልሉ ነዋሪዎች የነገውን የክልሉንና የሀገሪቱን እጣ ፈንታ ለመወሰን በምርጫው ዕለት ከጧቱ 12:00 ስዓት ጀምሮ በነቂስ በመውጣት ለምርጫው ስኬታማነት ያሳዩት ተሳትፎ በእጅጉ የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። የምርጫው ሂደትም እጅግ የተረጋጋ፣ ፍጹም ሰላማዊና የክልሉንና የሀገሪቷን መጻኢ የዴሞክራሲ ትግበራን በተግባር አጠናክሮ ያለፈ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ የነበረው ሂደት ፍጹም ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ላሳየው ቁርጠኝነትም ምክር ቤቱ ምስጋና ያቀርባል ብለዋል። ህዝብ የሰጠው ድምጽ የመጨረሻው የስልጣን ባለቤትነት መገለጫ በመሆኑ በቦርዱ የሚገለፀውን የምርጫ ውጤት በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ እንደሆነም የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢና የህዳሴ ፓርቲ የጋምቤላ ክልል አስተባባሪ መምህር ሻምበል ቶላ በበኩላቸው የምርጫው ሂደት ፍጹም ፍትሐዊ፣ ታዓማኒና ሰላማዊ እንደነበር ገልጸዋል። በምርጫው ህዝቡ በነፃነትና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ ላመነውና ይበጀኛል ለሚለው የፓለቲካ ፓርቲ ድምጹን መስጠቱን ጠቁመው፤ ሚዲያዎችም ገለልተኛ ሆነው ለምርጫው ስኬታማነት ለሰጡት ሽፋን ምስጋና ይገባል ብለዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ጸሐፊና በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፔን ኡጁሉ የዘንድሮው ምርጫ በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለውና እውነተኛ ዴሞክራሲ ጸንቶ የታየበት እንደነበር ገልጸዋል።
በምርጫው ያሳየነውን ተሳትፎ በሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ላይ ለመድገም የድርሻችንን እንወጣለን--የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች
Jun 4, 2026 501
ሚዛን አማን፣ ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፡- በምርጫው ያሳዩትን ተሳትፎ በሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ላይ ለመድገም በሚደረጉ ጥረቶች የድርሻቸውን እንደሚወጡ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ እንደገለጹት፤ በምርጫው ላይ ያሳየነውን የነቃ ተሳትፎ በልማት ተግባራት ላይ በመድገም ለሀገር ዕድገት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን። አቶ አህመድ ከድር የተባሉ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪ እንዳሉት ምርጫው እኛ ዜጎች ለኢትዮጵያ ከፍታ ያለንን ጽኑ ፍላጎትና ለዴሞክራሲ ሥርዓት መከበር ያለንን አቋም ያሳየንበት ነው። በምርጫው ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ የሌት ቁር የቀን ሀሩር ሳይበግረን ተግባራችንን እንደተወጣን ሁሉ በቀጣይም ለሁለንተናዊ ልማትና ዕድገት የበኩላችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን ብለዋል። ወይዘሮ ሰዋለም ጋሻው በበኩላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ህዝቡ በምርጫ ወቅት ያሳየው ንቁ ተሳትፎ በልማት ሊደግም እንደሚገባው ገልጸው ፓርቲዎችም የምርጫው ውጤት ምንም ይሁን ምን በፀጋ መቀበል እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። በምርጫ ወቅት ያሳየነውን የነቃ ተሳትፎ በሌሎች የልማት ሥራዎች በመድገም ለኢትዮጵያ ከፍታና አሸናፊነት እንሰራለን ያሉት ደግሞ መምህር መንዛ ዝትያብ (ዶ/ር) ናቸው። እንደ ሀገር አይቻልም የተባሉ በርካታ ጉዳዮችን በኢትዮጵያዊ ወኔና የአይበገሬነት መንፈስ እየቻልን አሳይተናል፤ በምርጫውም ይህንኑ ደግመናል፤ በልማቱ ደግሞ የተጀመሩ ጥረቶችን በትብብር እናጠናክራለን ብለዋል። ወጣት ዘማች ዳሩ በበኩሉ በራሳችን ፍላጎትና ተነሳሽነት በመምረጥ የዜግነት ግዴታችንን መወጣታችን ለዴሞክራሲ ባህል ማደግ ትልቅ ትርጉም አለው ሲል ገልጿል። በቀጣይም ለልማትና ዕድገታችን በጋራ በመንቀሳቀስ ለሰላማችን፣ ለልማትና የኑሮ ውድነት ተፅዕኖን ለመቀነስ ተግተን በመሥራት ለኢትዮጵያ ክብር በብርታት እንቆማለን ብሏል።
ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ የተጠቀሙበት ነው - የጋራ ምክር ቤቱ
Jun 4, 2026 478
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ የተጠቀሙበት መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለፀ። የጋራ ምክር ቤቱ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። በመግለጫው የምክር ቤቱ ተሰብሳቢ አቶ ጎበዜ አበራ እንደተናገሩት፤ በምርጫው ወቅት መራጩ ህዝብ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ድምፁን መስጠት መቻሉ የዘንድሮውን ሂደት ከሌሎች ወቅቶች የተለየ ያደርገዋል ብለዋል። ምርጫው ሕዝቡ ከማለዳው ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠበት መሆኑን አንስዋል። ህዝቡ በምርጫው ወቅት ያሳየው ቁርጠኝነት፣ የሀገር ማጽናት ጉዞውን እውን ለማድረግ ያለምንም እንከን እና በተረጋጋ ስሜት የፈለገውን ፓርቲ በፍትሃዊነት የመረጠበት መሆኑን ምክር ቤቱ ማረጋገጡንም አቶ ጎበዜ አክለው ገልጸዋል። ምክር ቤቱ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ወደፊት ይፋ የሚደረገውን የምርጫ ውጤት በፀጋ እንደሚቀበልና ከሚመሰረተው መንግስት ጋርም በሀገር ሰላምና ልማት ላይ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። በምርጫው የጋራ ምክር ቤቱ ተቀናጅቶ በመስራቱ እና መራጩ ህዝብ ሀገር ለማስቀጠል ያሳየው ቆራጥነት የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመው፤ ለምርጫው ሰላማዊነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝቡ የዴሞክራሲያዊ ባህል የዳበረበት መሆኑን እንዳሳየ የተናገሩት ደግሞ የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሻጌ ሻምባ ናቸዉ። ህዝቡ ለፈለገዉ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ሚናውን መወጣቱንም ጠቁመዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀሳባቸውን በነፃነት እንዲያቀርቡ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታና ሰፊ ምህዳር ለወደፊቱም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ገልፀዋል። የምክር ቤቱ ፀሐፊ አቶ ወልዴ ዳና በበኩላቸው ሕዝቡ ድምጹን ለፈለገው ፓርቲ በመስጠት የስልጣን ባለቤትነቱን በተግባር አረጋግጧል ብለዋል። ምክር ቤቱ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተባብሮ መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።
ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ አሳታፊና የኢትዮጵያን አሸናፊነት ያበሰረ ነው-የጋራ ምክር ቤቱ
Jun 4, 2026 585
አዲስ አበባ፣ግንቦት 27 /2018 (ኢዜአ):-ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ አሳታፊና የኢትዮጵያን አሸናፊነት ያበሰረ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በማካሄድ ባወጠው የአቋም መግለጫ፤ ምርጫው ሰላማዊ፣ዴሞክራሲያዊና አሳታፊ ሆኖ መካሄዱን ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ጸሐፊ አቶ ታሪኩ ድንበሩ የአቋም መግለጫውን ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ የዘንድሮው ምርጫ ከቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ እጅግ የተሻለ ሂደት የታየበት ነበር። የምርጫው ሂደትም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ህዝቡ በነጻነት ድምፅ የሰጠበት መሆኑን ገልጸዋል። የኦሮሚያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አሳታፊና ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ ታሪካዊና ሰላማዊ ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። በድምጽ መስጫው ዕለት መላው የክልሉ ህዝብ ከማለዳ ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በትዕግስት ተሰልፎ ድምጹን በመስጠት ያሳየው ጽናትና ቁርጠኝነት በእጅጉ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። በኦሮሚያ ክልል ምርጫው በስኬትና በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ዜጎች፣የጸጥታ አካላት፣ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ማኅበራትና ምርጫ አስፈጻሚዎች ምስጋናውን አቅርቧል። የጋራ ምክር ቤቱም በጠቅላላው የምርጫ ሂደት ውስጥ በትኩረት በመንቀሳቀስ የራሱን ድርሻ መወጣቱን በአቋም መግለጫቸው አረጋግጠዋል። ምርጫው በሰላማዊ፣በዴሞክራሲያዊ እና ስኬታማ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ የጋራ ምክር ቤቱ በትብብርና በቁርጠኝነት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ኢትዮጵያዊያን ከዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውጭ የስልጣን ባለቤት መሆን እንደማይቻል በተግባር ማሳየታቸውን አስረድተዋል።
ፖለቲካ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያና ሕዝቧ አሸናፊነት በተግባር የታየበት ነው
Jun 4, 2026 319
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያና ሕዝቦቿ አሸናፊነት በተግባር የታየበት መሆኑን ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት አስታወቀ። የትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የምርጫ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ምርጫው ስንሻው እንደገለጹት፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያውያንን እውነተኛ ፍላጎት ያንጸባረቀና የሀገሪቷን ታሪካዊ ጠላቶች ቅስም የሰበረ ክስተት ነው። ሕዝቡ ለሀገሩ ሰላምና ሉዓላዊነት ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበት መሆኑንም አክለው ገልጸዋል። ሀገርን ከጥፋት ጠብቆና ተቻችሎ መንግሥት የሚያቆመው ራሱ ሕዝቡ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዘንድሮ ምርጫ እውነተኛው አሸናፊ ሕዝቡ መሆኑን አስገንዝበዋል። ምርጫው እንዳይሳካ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ከፍተኛ ጫናዎች ቢቃጡም፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉንም ፈተናዎች በብስለትና በጽናት ተቋቁሞ መምረጡን ገልጸዋል። ሕዝቡ ሰላም ወዳድ በመሆኑ ምርጫው በስኬትና በድል ሊጠናቀቅ መቻሉን የገለጹት ኃላፊው፤ ለዚህም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሊመሰገንና ሊደነቅ እንደሚገባው ተናግረዋል። "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" ለሀገር ዘላቂ ሰላም የሚበጀው ሰላማዊ ትግል ብቻ ነው የሚለውን መርህ በመከተል ወደ ምርጫው መግባቱን የጠቀሱት ኃላፊው፤ በዚህም ፓርቲያቸው ከሕዝቡ ጋር በመሆን ታሪካዊ አሻራውን ማኖሩን አስገንዝበዋል። የዘንድሮው ምርጫ ዴሞክራሲያዊነት በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ ታዛቢዎች ጭምር እውቅና ያገኘ መሆኑን ያመለከቱት ኃላፊው አቶ ምርጫ፤ ለአብነትም የአፍሪካ ኅብረት፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ አሜሪካ እና ጃፓንን ጨምሮ በርካታ ሀገራትና ድርጅቶች የምስክርነት ቃላቸውን የሰጡበትና ኢትዮጵያውያን መቻላቸውን ለዓለም ያሳዩበት አጋጣሚ እንደሆነ አብራርተዋል። የምርጫው ሂደት ስኬታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ-ምርጫና በምርጫ ወቅት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ያከናወናቸው ተግባራት ለውጤቱ መገኘት ቁልፍ ሚና እንደነበራቸው ገልጸዋል፡፡ ለሂደቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የጸጥታ አካላት፣ ለሲቪል ማኅበራትና በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች ፓርቲው ያለውን ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት መፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Jun 4, 2026 436
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ቅድሚያ ለጎረቤት የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት መፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ምሁራን ገለጹ። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ለዓለም አቀፍ ንግድ ዋነኛ መተላለፊያ፣ የኃያልነት ፍትጊያ ማዕከልና ያልተነኩ ሃብቶች ወደ አሏቸው የአፍሪካ ሀገራት ዋና መግቢያ በር ሆኖ ያገለግላል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአፍሪካ ቀንድ ዓለም አቀፍ ፍላጎትና ተግዳሮት የሚንፀባረቅበት ስትራቲጂክ ቀጣና ነው። ለአብነትም አሜሪካ፣ ቻይና፣ የአውሮፓና የመካከለኛው ምስራቅ የባሕረ ሰላጤ ሀገራት ስትራቴጂክ ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም የትኩረት ማዕከላቸው ማሰሪያ አድርገው እንደሚመለከቱት ገልጸዋል። በሌላ መልኩም የሽብር ኃይሎች ደካማ የመንግሥት መዋቅሮችንና ድንበሮችን በመጠቀም ዓለም አቀፍ ትኩረት ለመሳብና የኢኮኖሚ ምንጭ ለማግኘት መሞከራቸው የቀጣናው ሁነኛ ስጋት አድርጓቸዋል ብለዋል። ኢትዮጵያም ቅድሚያ ለጎረቤት በሚሰጠው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ በኢኮኖሚ ትስስር እንዲሁም በሰላምና ደኅንነት ዘርፍ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን አንስተዋል። ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባሻገርም የተጋመደውን የቀጣናው ህዝብ በኃይል እና በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር ለቀጣናዊና አህጉራዊ የንግድ ስምምነት ትግበራ መሪ ሚናዋን እየተወጣች እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በትራንስፖርትና በዲጂታል መሰረተ ልማት፣ በወደብና የባሕር በር አማራጭ የማስፋት ስራ ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ውጤታማ አካሄድ እየተከተለች መሆኑን አስረድተዋል። የምስራቅ አፍሪካ የሽብር ኃይሎችን ህልም በማምከን የምታበረክተው ጉልህ አስተዋጽኦም ለሁለትዮሽና ባለ ብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ውጤታማነት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ብለዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን አንድነትና ጥንካሬ ከውጤታማ ዲፕሎማሲ ጋር በማጣጣም የባሕር በር ባለቤትነትና የማሪታይም ስትራቴጂን ማረጋገጥ እንዳለባት አስረድተዋል። ለዚህም ከቀጣናው ሀገራትና ኃያላኑ ጋር ስትራቴጂክ አጋርነትን በማጎልበት የህዝብ ለህዝብ መስተጋብርና ስብጥርን በትልቅ የዲፕሎማሲ መሳሪያነት መጠቀም እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያን የጎረቤት ሀገራት የብልጽግና ዋስትናነት የሚያጎላ የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት ስትራቴጂ ቀርጾ መተግበር እንደሚገባም ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ መከላከያ ኮሌጅ ተመራማሪና መምህር ፕሮፌሰር አየለ በከሪ በበኩላቸው፤ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሕዝቦች በቋንቋ፣ በሃይማኖትና በባሕል የጋራ ዕሴቶች የተጋመዱ ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብና የልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ኢኮኖሚ ውህደትን ለማፋጠን የምታደርገው ውጤታማ ጥረት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጸዋል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ቅቡልነት በማሳደግ የተፅዕኖ ፈጣሪነት አቅሟን ማጎልበት ያስቻለ ስኬት ማስገኘቱን ተናግረዋል። በቀጣይም የምስራቅ አፍሪካን የኢኮኖሚ ውህደት በማፋጠን፣ የውስጥና ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና ደኅንነትን በማስከበር ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎቷን ማረጋገጥ እንደሚኖርባት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው
Jun 4, 2026 509
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፤ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እና የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ ከአንጎላ ሪፐብሊክ፣ ከባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ እና ከኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጋር ያደረገቻቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ ሪፖርቶችና የውሳኔ ሃሳቦችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። እነዚህ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆች ለንግድና ኢንቨስትመንት፣ ለቱሪዝም፣ ለዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲሁም የአየር ትራንስፖርት መዳረሻዎችን ለማስፋፋት ያላቸውን ከፍተኛ ጠቀሜታ አብራርተዋል። በተጨማሪም ስምምነቶቹ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቁና በዘርፉ ያላትን ሚና በማጉላት ተጠቃሚነቷን የሚያሳድጉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። ምክር ቤቱም በቀረቡት ረቂቅ አዋጆች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ አዋጆቹን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። ከምክር ቤቱ አባላት በኩልም የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆቹ የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸው ተገልጿል። በሌላ በኩል፣ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመው ስምምነት ረቂቅ አዋጅም በምክር ቤቱ ጸድቋል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፤ ስምምነቱ የሀገሪቱን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን፣ ለዓሳ ሀብት ልማት፣ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ለማሳደግና በዘርፉ የግል ባለሀብቶችን ለመሳብ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማትን አቅም ለማሳደግና የምርምር ሥራዎችን ወደ ገበያ አውጥቶ ለማቅረብ ያለውን ጠቀሜታም አንስተዋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት በተፈረመው የስምምነት ረቂቅ አዋጅ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ፣ አዋጁን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫን ሰላምና ደኅንነት አፈፃፀም ገመገመ
Jun 4, 2026 463
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፀጥታና ደኅንነት አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መስሪያ ቤት ተገምግሟል። በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የጋራ ግብረ ኃይሉ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫው ወቅትና ከምርጫ በኋላ ያሉ ስራዎችን እንደ ሀገር ዕቅድ አውጥቶ በቅንጅት በመመራቱ፤ በተግባር የተፈተሸ፣ የተናበበና ሰላምን ለማፅናት ጀግንነት የታየበት ተግባር በመፈፀሙ ምርጫው በሰላም ሊጠናቀቅ ችሏል ብለዋል። ኮሚሽነር ጀነራሉ አያይዘውም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶት በፀጥታና ደህንነት ተቋማት ላይ በተሰራው ሪፎርም አሁን ላይ በተጨባጭ ትላልቅ ተልዕኮዎችን መሸከም የሚችሉ የፀጥታ ተቋማት መፈጠራቸውን በምርጫው ላይ የተመዘገበው ውጤት ማሳያ ነው ብለዋል። የጋራ ግብረ-ኃይሉ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ጠላቶች የተቀናጀውን ከፍተኛ ሴራ ያከሸፈ፣ ያመከነና የሀገርን ሉዓላዊነት ያረጋገጠ፤ የሪፎርሙ ውጤት በተግባር የተለካበትና የታየበት መሆኑንም ገልፀዋል። እንደ ፀጥታ ተቋም መኩራትና መመካት ያለብን በኢትዮጵያ ህዝብ ነው ያሉት ኮሚሽነር ጀነራል በሀገራችን ላይ እየሆነ ያለውን ተረድቶ፣ ሁሉንም በሚዛን አስቀምጦ፣ የምርጫው ቀን ሲደርስ ለሁላችንም ትምህርት ያስተላለፈ የሀገር አንድነት እና ሉአላዊነትን ያጸና የኢትዮጵያ ህዝብ ታላቅ ህዝብ መሆኑን ያረጋገጠበት እንዲሁም ከዚህ በኋላ መንግስት በካርድ እንጂ በጥይት አይሆንም የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ምርጫ መሆኑን ገልፀዋል። በቀጣይም በሽብርተኞችና በፅንፈኞች ላይ የተጀመረው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለፀው የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይሉ፤ የምርጫው ውጤት ታውቆ አዲስ የመንግስት ምስረታ እስከሚከናወን እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ያሉ ሕዝባዊና መንግስታዊ ሁነቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ የፀጥታ ሥራው ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቅጣጫ አስቀምጧል።
የምርጫ ሂደቱ እውነተኛ ዴሞክራሲ በተግባር ፀንቶ የታየበት ነው- የጋራ ምክር ቤቱ
Jun 4, 2026 529
ጋምቤላ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፡- የምርጫ ሂደቱ ቅቡልነት ያለውና እውነተኛ ዴሞክራሲ በተግባር ጸንቶ የታየበት መሆኑን በጋምቤላ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ። በክልሉ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ በማስመልከት ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢና የኢዜማ ጋምቤላ ቅርንጫፍ ምክትል መሪ ኮማንደር ጋትቤል ቦል፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። የክልሉ ነዋሪዎች የነገውን የክልሉንና የሀገሪቱን እጣ ፈንታ ለመወሰን በምርጫው ዕለት ከጧቱ 12:00 ስዓት ጀምሮ በነቂስ በመውጣት ለምርጫው ስኬታማነት ያሳዩት ተሳትፎ በእጅጉ የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። የምርጫው ሂደትም እጅግ የተረጋጋ፣ ፍጹም ሰላማዊና የክልሉንና የሀገሪቷን መጻኢ የዴሞክራሲ ትግበራን በተግባር አጠናክሮ ያለፈ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ የነበረው ሂደት ፍጹም ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ላሳየው ቁርጠኝነትም ምክር ቤቱ ምስጋና ያቀርባል ብለዋል። ህዝብ የሰጠው ድምጽ የመጨረሻው የስልጣን ባለቤትነት መገለጫ በመሆኑ በቦርዱ የሚገለፀውን የምርጫ ውጤት በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ እንደሆነም የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢና የህዳሴ ፓርቲ የጋምቤላ ክልል አስተባባሪ መምህር ሻምበል ቶላ በበኩላቸው የምርጫው ሂደት ፍጹም ፍትሐዊ፣ ታዓማኒና ሰላማዊ እንደነበር ገልጸዋል። በምርጫው ህዝቡ በነፃነትና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ ላመነውና ይበጀኛል ለሚለው የፓለቲካ ፓርቲ ድምጹን መስጠቱን ጠቁመው፤ ሚዲያዎችም ገለልተኛ ሆነው ለምርጫው ስኬታማነት ለሰጡት ሽፋን ምስጋና ይገባል ብለዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ጸሐፊና በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፔን ኡጁሉ የዘንድሮው ምርጫ በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለውና እውነተኛ ዴሞክራሲ ጸንቶ የታየበት እንደነበር ገልጸዋል።
በምርጫው ያሳየነውን ተሳትፎ በሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ላይ ለመድገም የድርሻችንን እንወጣለን--የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች
Jun 4, 2026 501
ሚዛን አማን፣ ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፡- በምርጫው ያሳዩትን ተሳትፎ በሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ላይ ለመድገም በሚደረጉ ጥረቶች የድርሻቸውን እንደሚወጡ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ እንደገለጹት፤ በምርጫው ላይ ያሳየነውን የነቃ ተሳትፎ በልማት ተግባራት ላይ በመድገም ለሀገር ዕድገት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን። አቶ አህመድ ከድር የተባሉ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪ እንዳሉት ምርጫው እኛ ዜጎች ለኢትዮጵያ ከፍታ ያለንን ጽኑ ፍላጎትና ለዴሞክራሲ ሥርዓት መከበር ያለንን አቋም ያሳየንበት ነው። በምርጫው ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ የሌት ቁር የቀን ሀሩር ሳይበግረን ተግባራችንን እንደተወጣን ሁሉ በቀጣይም ለሁለንተናዊ ልማትና ዕድገት የበኩላችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን ብለዋል። ወይዘሮ ሰዋለም ጋሻው በበኩላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ህዝቡ በምርጫ ወቅት ያሳየው ንቁ ተሳትፎ በልማት ሊደግም እንደሚገባው ገልጸው ፓርቲዎችም የምርጫው ውጤት ምንም ይሁን ምን በፀጋ መቀበል እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። በምርጫ ወቅት ያሳየነውን የነቃ ተሳትፎ በሌሎች የልማት ሥራዎች በመድገም ለኢትዮጵያ ከፍታና አሸናፊነት እንሰራለን ያሉት ደግሞ መምህር መንዛ ዝትያብ (ዶ/ር) ናቸው። እንደ ሀገር አይቻልም የተባሉ በርካታ ጉዳዮችን በኢትዮጵያዊ ወኔና የአይበገሬነት መንፈስ እየቻልን አሳይተናል፤ በምርጫውም ይህንኑ ደግመናል፤ በልማቱ ደግሞ የተጀመሩ ጥረቶችን በትብብር እናጠናክራለን ብለዋል። ወጣት ዘማች ዳሩ በበኩሉ በራሳችን ፍላጎትና ተነሳሽነት በመምረጥ የዜግነት ግዴታችንን መወጣታችን ለዴሞክራሲ ባህል ማደግ ትልቅ ትርጉም አለው ሲል ገልጿል። በቀጣይም ለልማትና ዕድገታችን በጋራ በመንቀሳቀስ ለሰላማችን፣ ለልማትና የኑሮ ውድነት ተፅዕኖን ለመቀነስ ተግተን በመሥራት ለኢትዮጵያ ክብር በብርታት እንቆማለን ብሏል።
ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ የተጠቀሙበት ነው - የጋራ ምክር ቤቱ
Jun 4, 2026 478
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ የተጠቀሙበት መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለፀ። የጋራ ምክር ቤቱ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። በመግለጫው የምክር ቤቱ ተሰብሳቢ አቶ ጎበዜ አበራ እንደተናገሩት፤ በምርጫው ወቅት መራጩ ህዝብ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ድምፁን መስጠት መቻሉ የዘንድሮውን ሂደት ከሌሎች ወቅቶች የተለየ ያደርገዋል ብለዋል። ምርጫው ሕዝቡ ከማለዳው ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠበት መሆኑን አንስዋል። ህዝቡ በምርጫው ወቅት ያሳየው ቁርጠኝነት፣ የሀገር ማጽናት ጉዞውን እውን ለማድረግ ያለምንም እንከን እና በተረጋጋ ስሜት የፈለገውን ፓርቲ በፍትሃዊነት የመረጠበት መሆኑን ምክር ቤቱ ማረጋገጡንም አቶ ጎበዜ አክለው ገልጸዋል። ምክር ቤቱ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ወደፊት ይፋ የሚደረገውን የምርጫ ውጤት በፀጋ እንደሚቀበልና ከሚመሰረተው መንግስት ጋርም በሀገር ሰላምና ልማት ላይ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። በምርጫው የጋራ ምክር ቤቱ ተቀናጅቶ በመስራቱ እና መራጩ ህዝብ ሀገር ለማስቀጠል ያሳየው ቆራጥነት የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመው፤ ለምርጫው ሰላማዊነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የህዝቡ የዴሞክራሲያዊ ባህል የዳበረበት መሆኑን እንዳሳየ የተናገሩት ደግሞ የጋራ ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሻጌ ሻምባ ናቸዉ። ህዝቡ ለፈለገዉ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ሚናውን መወጣቱንም ጠቁመዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀሳባቸውን በነፃነት እንዲያቀርቡ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታና ሰፊ ምህዳር ለወደፊቱም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ገልፀዋል። የምክር ቤቱ ፀሐፊ አቶ ወልዴ ዳና በበኩላቸው ሕዝቡ ድምጹን ለፈለገው ፓርቲ በመስጠት የስልጣን ባለቤትነቱን በተግባር አረጋግጧል ብለዋል። ምክር ቤቱ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተባብሮ መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።
ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ አሳታፊና የኢትዮጵያን አሸናፊነት ያበሰረ ነው-የጋራ ምክር ቤቱ
Jun 4, 2026 585
አዲስ አበባ፣ግንቦት 27 /2018 (ኢዜአ):-ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ አሳታፊና የኢትዮጵያን አሸናፊነት ያበሰረ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በማካሄድ ባወጠው የአቋም መግለጫ፤ ምርጫው ሰላማዊ፣ዴሞክራሲያዊና አሳታፊ ሆኖ መካሄዱን ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ጸሐፊ አቶ ታሪኩ ድንበሩ የአቋም መግለጫውን ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ የዘንድሮው ምርጫ ከቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ እጅግ የተሻለ ሂደት የታየበት ነበር። የምርጫው ሂደትም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ህዝቡ በነጻነት ድምፅ የሰጠበት መሆኑን ገልጸዋል። የኦሮሚያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አሳታፊና ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ ታሪካዊና ሰላማዊ ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። በድምጽ መስጫው ዕለት መላው የክልሉ ህዝብ ከማለዳ ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በትዕግስት ተሰልፎ ድምጹን በመስጠት ያሳየው ጽናትና ቁርጠኝነት በእጅጉ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል። በኦሮሚያ ክልል ምርጫው በስኬትና በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ዜጎች፣የጸጥታ አካላት፣ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ማኅበራትና ምርጫ አስፈጻሚዎች ምስጋናውን አቅርቧል። የጋራ ምክር ቤቱም በጠቅላላው የምርጫ ሂደት ውስጥ በትኩረት በመንቀሳቀስ የራሱን ድርሻ መወጣቱን በአቋም መግለጫቸው አረጋግጠዋል። ምርጫው በሰላማዊ፣በዴሞክራሲያዊ እና ስኬታማ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ የጋራ ምክር ቤቱ በትብብርና በቁርጠኝነት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ኢትዮጵያዊያን ከዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውጭ የስልጣን ባለቤት መሆን እንደማይቻል በተግባር ማሳየታቸውን አስረድተዋል።
ማህበራዊ
ኢትዮጵያ ከአበረታች ቅመሞች ነጻ የሆነ ስፖርት ለመገንባት የጸና አቋም አላት
Jun 4, 2026 379
አዳማ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ አበረታች ቅመሞችን በመዋጋት ንጹህ ስፖርት ለመገንባት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን የኢትዮጵያ የፀረ አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መኮንን ይደርሳል ገለጹ። ባለስልጣኑ በስፖርት ውስጥ የተከለከሉ አበረታች ቅመሞች (Doping) እና ዘዴዎችን አስመልክቶ ለስፖርት ጋዜጠኞች ያዘጋጀው የስልጠናና የውይይት መድረክ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። ስልጠናው የተዘጋጀው ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር ጋር በመተባበር ነው። የመድረኩ ዋና ዓላማ፥ ዶፒንግ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመከላከል ባለስልጣኑ ለጀመረው ስራ ስኬት የስፖርት ጋዜጠኞች የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ማስቻል ነው። አቶ መኮንን ይደርሳል ባለስልጣኑ ከቁጥጥር፣ ምርመራ እና ህጋዊ እርምጃ ባለፈ ሰፊ የንቅናቄ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝና በተለይም ለስፖርተኞች ተከታታይ ስልጠናዎችን በመስጠት ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ አበረታች ቅመሞች በትምህርት ስርዓት ውስጥ መካተቱ መንግስት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይና ይህም በዘላቂነት ንጹህ ስፖርትን ለመፍጠር እየተከናወነ ላለው ስራ ወሳኝ ሚና ይጫወታል ብለዋል። የስፖርት ፌዴሬሽኖች እና የስፖርት ስልጠና ማዕከላት የስልጠና ማዕቀፎችን በማዘጋጀት ለስፖርተኞች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም አንስተዋል። ከምርመራ እና ቁጥጥር ጋር በተገናኘም የአበረታች ቅመሞች ተጋላጭነት ያለባቸው የስፖርት አይነቶችን በመለየት ተደራሽነትን ለማስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በራሷ ምርመራ ማድረግ የሚያስችል አቅም እንድትፈጥር የተጀመሩ ስራዎች በጥሩ መስመር ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው በቅርቡ የምርመራ ላቦራቶሪ ስራ ለማስጀመር እቅድ መያዙን ጠቁመዋል። አበረታች ቅመሞችን የሚጸየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር እና የንጹህ ስፖርት እሳቤ እንዲሰርጽ በማድረግ ረገድ የሚዲያው ሚና ወሳኝ መሆኑንም አመልክተዋል። የኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ንዋይ ይመር ጋዜጠኞች በአበረታች ቅመሞች ዙሪያ ስነምግባርን ባከበረ መልኩ ዘገባዎችን ማቅረብ እንዳለባቸው አመልክተዋል። ጋዜጠኞች በተከለከሉ አበረታች ቅመሞች እና በተፈጥሯዊ አቅም የሚገኙ ውጤቶች መካከል ያለውን ግልጽ ልዩነት ማወቅ እንዳለባቸውም ነው የገለጹት። አንድ ስፖርተኛ እስካልተረጋገጠ ድረስ ንጹህ የመሆን መብቱን (Presumption of Innocence) ጠብቆ መዘገብ እንዲሁም ታዳጊ ስፖርተኞች ህግና ስነ-ልቦናዊ ጥበቃ ሊደረግላቸው የሚገባ መሆኑን ከግምት ማስገባት እንደሚያስፈልግም አመልክተዋል። በአጠቃላይ ጋዜጠኞች ሙያዊ ስነምግባርን አክብሮ በተከለከሉ የአበረታች ቅመሞች መከላከልና ቁጥጥር ላይ ኃላፊነት በተሞላበትና ብሔራዊ ፍላጎት ባማከለ መልኩ ገንቢ ሚና መጫወት እንደሚገባቸው አሳስበዋል። በመድረኩ የተሳተፉ የስፖርት ጋዜጠኞች በበኩላቸው ስልጠናው ወቅቱን የጠበቀና የፀረ አበረታች ቅመሞች ስራዎች ላይ ግንዛቤ በማሳደግ ማህበረሰቡን ለማስተማር መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያስገነባቸውን መኖሪያ ቤቶች ለአቅመ ደካማ ወገኖች አስረከበ
Jun 4, 2026 365
አምቦ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፦ የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሃጫሉ ሁንዴሳ ካምፓስ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያስገነባቸውን የመኖሪያ ቤቶች ለአቅመ ደካማ ወገኖች አስረከበ። ዩኒቨርሲቲው ቤቶቹን በ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ ማስገንባቱንም የቤቶቹ ርክክብ በሚከናወንበት ወቅት ተገልጿል። በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሃጫሉ ሁንዴሳ ካምፓስ ዲን ኢንጂነር ወዬሳ አራርሳ በወቅቱ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት አቅም የሌላቸው ወገኖችን በበጎ ፈቃድ ተግባራት ተጠቃሚ እያደረገ ነው። በዚህም ዩኒቨርሲቲው በበጎፈቃድ ያስገነባቸውን መኖሪያ ቤቶች ለአቅመ ደካማ ወገኖች ዛሬ አስረክቧል ብለዋል። ለቤቶቹ ግንባታም ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና መምህራን እንዲሁም ከተማሪዎች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መዋጮ መሰብሰቡን ጠቁመዋል። በቀጣይም ዩኒቨርሲቲው የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል የህብረተሰቡን ችግር ለመፍታት እንደሚተጋም አረጋግጠዋል። በከተማዋ የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ማህበራዊ ችግሮች እንዲቃለሉ ማገዛቸውን ያነሱት ደግሞ የአምቦ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃጫሉ ገመቹ ናቸው። የበጎ ፈቃድ ተግባራቱ ለተቸገሩ ወገኖች ለመድረስ እንዳስቻሉ ገልጸው፤ የሕብረተሰቡ የእርስ በርስ የመተጋገዝ እሴት እንዲጎለብትም አድርገዋል ብለዋል። የአምቦ ከተማ አስተዳደር ሴቶች እና ሕፃናት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኢሊሌ ተስፋዬ በበኩላቸው የአምቦ ዩኒቨርሲቲ በከተማዋ በሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ለአቅመ ደካማ እናቶች ቤት ሰርቶ ከማስረከብ ባሻገር ለተቸገሩ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የመኖሪያ ቤት ከተረከቡ ነዋሪዎች መካከል ሶስት ልጆቻቸውን ይዘው ደሳሳ ቤት ተከራይተው ይኖሩ የነበሩት ወይዘሮ አዳነች ጭምሳ ይገኙበታል። ተከራይተው የሚኖሩበት ቤት የሚያፈስ በመሆኑ በክረምት ወቅት ለመኖር አስቸጋሪ ጊዜን ማሳለፋቸውን ተናግረው አሁን ዩኒቨርሲቲው የቤት ባለቤት ስላደረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል። ወይዘሮ ብርሃኔ ገመቹ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም አምስት ልጆቻቸውን ይዘው ጎዳና ላይ ይኖሩ እንደነበር ጠቁመው የተረከቡት ቤት ይህንን ችግር እንዳስወገደላቸው ተናግረዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ እሳቸውን ከችግር እንዳወጣቸው ሁሉ ለሌሎች ለተቸገሩ ወገኖች እንዲደርስም ጠይቀዋል።
በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የመጠጥ ውሃ ችግርን በዘላቂነት መፍታት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Jun 4, 2026 419
ሰቆጣ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የመጠጥ ውሃ ችግርን በዘላቂነት መፍታት የሚያስችሉ የልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የአስተዳደሩ ውሃና ኢነርጅ መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ግንባታ ክትትል ባለሞያ ታደሰ አዳነ፤ በመንግስት በተሰጠው ልዩ ትኩረት አካባቢው የውሃ ሃብት አማራጮችን በማልማት ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሁ መሰረትም በበጀት ዓመቱ 56 አዲስ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶቸን ለመገንባት ታቅዶ እስካሁን 29 የሚሆኑት ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት በቅተዋል ብለዋል። በእቅዱ መሰረት ሌሎች የግንባታ ስራዎችንም በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የተገነቡ የውሃ ፕሮጀክቶች የተሟላና ዘላቂ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻልም ህብረተሰቡን ያሳተፈ የአጠቃቀምና አስተዳደር አገልግሎት እየተከናወነ መሆኑንም አንስተዋል። የመጠጥ ውሃ ችግርን በዘላቂነት መፍታት የሚያስችሉ የልማት ስራዎች በአስተዳደሩ በስፋት እየተከናወኑ መሆኑንና ተጠናከረው የሚቀጥሉ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ አህጉራዊ የማይበገር የጤና ስርዓትን ለመገንባት መሪ ሚናዋን አጠናክራ ትቀጥላለች-ዶክተር ደረጀ ዱጉማ
Jun 4, 2026 338
አዲስ አበባ፤ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ አህጉራዊ የማይበገር የጤና ስርዓትን ለመገንባት መሪ ሚናዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎትና በጤናው ዘርፍ ባስመዘገበቻቸው ተምሳሌታዊ ስኬቶች በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው መሾማቸው ይታወቃል። የአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ከጤና ሚኒስቴርና ከአህጉራዊ የጤና ተቋማት ጋር በመተባበር በአፍሪካ የጤና ደህንነትና የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ ላይ ያተኮረ አህጉራዊ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የምክክሩ ዋና ዓላማ የአፍሪካ ሀገራት የቅድመ በሽታ መከላከል አቅምን ለማሳደግ ትብብራቸውን ለማጠናከር ነው። ቅድመ በሽታ መከላከል ለኢትዮጵያ የጤና ስርዓት የማዕዘን ድንጋይ መሆኑን በማንሳት፥ በአሁኑ ወቅት በመላ ሀገሪቱ ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም የኢትዮጵያን የጤና ስርዓት በከፍተኛ ደረጃ እንዳሻሻለውና በተለይ ደግሞ በእናቶችና ህጻናት ሞት ቅነሳ የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። ለዚህ ውጤት መገኘት ከመንግስት ቁርጠኝነት በተጨማሪ የህብረተሰቡ ተሳትፎ እና የአጋር አካላት ትበብር ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከቅድመ በሽታ መከላከል ባሻገር አክሞ የማዳን አቅሟ ከጊዜ ወደ ጊዜ በእጅጉ እያደገ መምጣቱን አመላክተዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከሰቱ ወረርሽኞችን በራስ አቅም በመቆጣጠር ረገድ አድናቆትን ያተረፉ ተግባራትን ማከናወኗን ጠቁመዋል። አፍሪካውያን የበሽታ ቅድመ መከላከልን ጨምሮ የጤና ደህንነትን በማረጋገጥ የማይበገር የጤና ስርዓት ለመገንባት እርስ በርስ መተባበር እንዳለባቸው አንስተዋል። ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ ያላትን የበሽታ ቅደመ መከላከል ልምድ በማካፈል አህጉራዊ የማይበገር የጤና ስርዓት ለመገንባት መሪ ሚናዋን ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል። የአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ምክትል ዋና ዳይሬክተር ራጂ ታጁዲን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ናቸው ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት በተለይ በበሽታ ቅድመ መከላከል ላይ ትበብራቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በማንሳት፥ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከሉ ትብብሩን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው
Jun 4, 2026 509
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፤ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እና የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ ከአንጎላ ሪፐብሊክ፣ ከባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ እና ከኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጋር ያደረገቻቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ ሪፖርቶችና የውሳኔ ሃሳቦችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። እነዚህ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆች ለንግድና ኢንቨስትመንት፣ ለቱሪዝም፣ ለዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲሁም የአየር ትራንስፖርት መዳረሻዎችን ለማስፋፋት ያላቸውን ከፍተኛ ጠቀሜታ አብራርተዋል። በተጨማሪም ስምምነቶቹ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቁና በዘርፉ ያላትን ሚና በማጉላት ተጠቃሚነቷን የሚያሳድጉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። ምክር ቤቱም በቀረቡት ረቂቅ አዋጆች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ አዋጆቹን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። ከምክር ቤቱ አባላት በኩልም የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆቹ የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸው ተገልጿል። በሌላ በኩል፣ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመው ስምምነት ረቂቅ አዋጅም በምክር ቤቱ ጸድቋል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፤ ስምምነቱ የሀገሪቱን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን፣ ለዓሳ ሀብት ልማት፣ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ለማሳደግና በዘርፉ የግል ባለሀብቶችን ለመሳብ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማትን አቅም ለማሳደግና የምርምር ሥራዎችን ወደ ገበያ አውጥቶ ለማቅረብ ያለውን ጠቀሜታም አንስተዋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት በተፈረመው የስምምነት ረቂቅ አዋጅ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ፣ አዋጁን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
ስምምነቱ የአርብቶ አደሮችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የአደጋ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችል ነው
Jun 4, 2026 311
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ልማት ባንክ መካከል የተፈረመው ስምምነት የአርብቶ አደሮችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የአደጋ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችል መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ23ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል። በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) በኢትዮጵያና በአፍሪካ ልማት ባንክ መካከል የተፈረመው የአርብቶ አደሮች የኑሮ ዘይቤ ማሻሻያ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል የብድር ስምምነት እና በኢትዮጵያና በዓለም አቀፍ የልማት ማህበር 6ኛው ምዕራፍ የልማታዊ ሴፍትኔት ማስፈጸሚያ ፕሮጀክት የተደረገ የብድር ስምምነት ረቂቅ አዋጆችን አስፈላጊነት በተመለከተ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ አቅርበዋል። የአርብቶ አደሮች የምግብና የኑሮ ዘይቤ ማሻሻያ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውለው የብድር ስምምነት ከኢትዮጵያ የብድር ስትራቴጂ ጋር የሚጣጣም ነው ብለዋል። ስምምነቱ የአርብቶ አደሮችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ፣ ለግብርና፣ ለመስኖ ልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና የአደጋ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ለውሃ መሰረተ ልማት፣ ለእንስሳት ጤና አገልግሎት፣ ለዘላቂ የመሬት አያያዝ፣ ለአየር ትንበያ ጣቢያዎችና ለሌሎች መሰረተ ልማቶች ማስፋፊያ እንደሚውልም ጠቅሰዋል። ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ረቂቅ አዋጁን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። በሌላ በኩል በኢትዮጵያና በዓለምአቀፍ የልማት ማህበር 6ኛው ምዕራፍ የልማታዊ ሴፍትኔት ማስፈጸሚያ ፕሮጀክት የተደረገው የብድር ስምምነት ሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በኑሮ ማሻሻል፣ በምግብ ዋስትና እና በማህበራዊ ጥበቃ ሰርዓት እየተከናወኑ ካሉ ብሔራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ጋር የተናበበ በመሆኑ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል። የምክር ቤቱ አባላት የብድር ስምምነቶቹ በግብርና፣ በመስኖ ልማት፣ በአየር ንብረት ለውጥ መቋቋምና የአደጋ ተጋላጭነትን በመቀነስ የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል የተጀመሩ ሥራዎችን እንደሚያጠናክሩ ጠቁመዋል። ስምምነቶቹ በአግባቡ እንዲተገበሩና የታለመውን ግብ እንዲያሳኩ ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል። ምክር ቤቱ የስምምነት ረቂቅ አዋጆች ላይ በዝርዝር በመወያየት በአብላጫ ድምጽ አጽድቋቸዋል። በሌላ በኩል የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን፣ የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ረቂቅ አዋጅን፣ የምግብ ስርዓትና ስርዓተ ምግብ ረቂቅ አዋጅን፣ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅን እና የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ ረቂቅ አዋጆች ቀርበው ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች ተመርተዋል።
በበጀት ዓመቱ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመሩ ተግባራትን ለማጠናቀቅ በትኩረት ይሰራል
Jun 4, 2026 310
አዲስ አበባ፤ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፦በ2018 በጀት ዓመት የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመሩ ተግባራትን ለማጠናቀቅ በትኩረት ይሰራል ሲሉ በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። በሀረሪ ክልል በ2018 በጀት ዓመት ቀሪ ጊዜያት በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ውይይት ተደርጓል። በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በውይይቱ ላይ እንደገለፁት፥ የበጀት ዓመቱ ቀጣይ እቅዶችን በስኬት ለማጠናቀቅ በትኩረት ይሰራል። በመሆኑም ተቋማት የማህበረሰቡን የመልካም አስተዳደርና ልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የጀመሯቸውን ተግባራት በቀሪ ጊዜያት ለማጠናቀቅ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ገልፀዋል። በተለይም በቱሪዝም ልማት፣የትምህርትና የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትና በኮሪደር ልማት ላይ የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ገልፀዋል። የሌማት ትሩፋት እና የከተማ ግብርና ስራዎችን በማጠናከር የግብርና ምርትና ምርታማነትን የማሳደጉ ስራም በበጀት ዓመቱ በልዩ ትኩረት ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። ለዜጎች የስራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት በመስጠት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው እንዲጎለብት ለማድረግ በቀጣይ ርብርብ እንደሚደረግም ገልፀዋል።
የባህርዳር ከተማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ከጣና ውበት ጋር በማሰናሰል የተገነባ ዘመን ተሻጋሪ የቱሪዝም ሃብት ነው
Jun 4, 2026 317
ባህር ዳር ፤ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ) ፡-የባህርዳር ከተማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ከጣና ውበት ጋር በማሰናሰል የተገነባ ዘመን ተሻጋሪ የቱሪዝም ሃብት መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ። ከተማዋ በተፈጥሮ የታደለችና አባይና ጣናን ተንተርሳ መመስረቷ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ይበልጥ ውበቷ እየተገለጠ እንድትመጣ አድርጓታል። የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ትዕግስት አበጀ፤ ባህር ዳር ከተማ በተፈጥሮ የታደለች መሆኗን ተከትሎ ባለፉት ጥቂት አመታት ደግሞ ውበቷን የገለጡ የልማት ስራዎች መከናወናቸው ውበቷን ያጎላው መሆኑን ገልጸዋል። በከተማዋ ከኮሪደር ልማቱ በተጨማሪ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተው ውበቷና ድምቀቷ ይበልጥ እየጨመረ መጥቷል ብለዋል። የባህር ዳር የኮሪደር ልማት ከጣና ሃይቅ ጋር በተሳሰረ መልኩ የተገነባ መሆኑም ከተማዋን ልዩ ገፅታ ስለማጎናፀፉ አንስተዋል። እንደ አጠቃላይ የባህርዳር ከተማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ከጣና ውበት ጋር በማሰናሰል የተገነባ ዘመን ተሻጋሪ የቱሪዝም ሃብት መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ ወጣት ደጀኔ አለምነው፤ የባህር ዳር ውበትና የቱሪዝም መስህብነት ከእለት ወደ እለት እያደገ መሆኑን ተናግሯል። በከተማዋ የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ የተለያዩ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ የአረንጓዴ ልማት፣ የእግረኛ፣ የሳይክል መንገዶችና ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራቶች መዘጋጀታቸው ከተማዋን ለነዋሪዎችና ለቱሪስቶች ምቹ አድርጓታል ብሏል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ገብረስላሴ ሳህሌ፤ ከባህር ዳር ከተማ ለዘመናት ተከልሎ የነበረው የጣና ሃይቅ ውበት በኮሪደር ልማት መገለጡ ለነዋሪዎችም ይሁን ለጎብኝው ደስታ ፈጥሯል ብለዋል። አሁን ላይ ወደ ባህር ዳር ጎራ የሚል ሁሉ ከተማዋን እየጎበኙ የጣናን ውበት እያደነቁ የሚደሰቱበት ስለመሆኑ ተናግረዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በባህር ዳር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎችም የተገነቡ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች የሚደነቁ ናቸው ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ባንኩ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደራሽ በማድረግ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማረጋገጥ አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል
Jun 4, 2026 179
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደራሽ በማድረግ የደንበኞቹን ፍላጎት ከማረጋገጥ አንጻር አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ (Visa) ኩባንያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን አዲስ የግብይትና የክፍያ ካርድ አገልግሎት ዛሬ ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ፤ ባንኩ በዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህም የባንኩ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሼባማይልስ (ShebaMiles) ደንበኞች በጋራ ሊጠቀሙበት የሚችሉትን የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ (CBE-ET Cobranded Visa Prepaid Card) ዛሬ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ የሼባማይልስ አባላት የኢ-ኮሜርስ ክፍያዎችን በቀላሉ መፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፥ በሚያደርጉት ግብይትም የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ በር ይከፍታል ብለዋል። ደንበኞች በካርዱ ግብይት በሚፈጽሙበት ወቅት የሼባማይልስ ነጥቦችን የሚያከማቹ ሲሆን፥ የተሰበሰቡትን ነጥቦች ለአውሮፕላን ትኬት መግዣና ለሌሎች የሼባማይልስ ማበረታቻ ጥቅማጥቅሞች ማዋል እንደሚችሉ አብራርተዋል። የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያዴቻ በበኩላቸው፤ የዚህ የቪዛ ካርድ ይፋ መሆን ለአየር መንገዱ የሼባማይልስ ደንበኞች ዘመናዊና የተቀላጠፈ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
በክልሉ ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ
Jun 4, 2026 330
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለፁ፡፡ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ሀዋሳን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ጎብኝተዋል፡፡ ርእሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ በክልሉ የሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በይፋ ሥራ ከጀመረ በኋላ ባሉት ዘጠኝ ወራት ከ50 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት መሰጠቱን ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ተገልጋዮች በማእከሉ በተሰጣቸው አገልግሎት እርካታ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። አገልግሎቱን ወደ ሁሉም አካባቢዎች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በቅርቡ ስራ የጀመረውን የሀዋሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የክልሉ ከተሞችም አገልግሎቱን በማስፋት ህዝቡ ሳይንገላታ የተቀላጠፈ አገልግሎት በቀላሉ እንዲያገኝ ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን ገልፀው በግንባታ ላይ ያሉና በአጭር ጊዜ ውስጥ ለአገልግሎት የሚበቁ ማዕከላት መኖራቸውን አመልክተዋል፡፡ በሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመገኘት ከተገለገሉ ነዋሪዎች መካከል አቶ ወንደሰን አሸቴ፤በማዕከሉ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ወደ ማዕከሉ በመጡ በ30 ደቂቃ ውስጥ የሚፈልጉትን አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ማግኘታቸውን ገልፀዋል፡፡ በማዕከሉ የአሻራ አገልግሎት እንዳገኙ የተናገሩት አቶ ፈጠነ አድማሱ በበኩላቸው በአጭር ጊዜ የተቀላጠፈ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ ጉዳያቸውን በጊዜ ጨርሰው ወደ ሌላ የዕለት ተግባራቸው መሄድ እንደቻሉም አስረድተዋል፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ግልፅና የተቀላጠፈ አገልግሎት ማግኘት መቻሉ በራሱ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝታቸው የሲዳማና የሀዋሳ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ማዕከላትን እንዲሁም በወንዶ ገነትና ለኩ ከተሞች እየተገነቡ ያሉ ማዕከላትን የተመለከቱ ሲሆን ሌሎች የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን የዜጎችን እንግልት እያስቀረ ነው
Jun 4, 2026 381
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን የዜጎችን እንግልት እያስቀረ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የተገነባውን መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት መርቀው ከፍተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ እንደገለጹት፤ በአዲስ አበባ የመንግሥት አገልግሎቶችን ፍትሀዊነት የሚያረጋግጥ ቀልጣፋና ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጥ ምኅዳር እየተፈጠረ ነው። የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ህብረተሰቡ የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያጋጥመውን የመልካም አስተዳደር ችግር በማስቀረት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትንም ከአንድ ማዕከል ወደ ተንቀሳቃሽ በማሸጋገር የተደራሽነት አድማሱን የማስፋት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከተማ አስተዳደሩ የአዲስ አበባን የመንግሥት አገልግሎቶች ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የወሰደውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አስረድተዋል። ለምረቃ የበቃው የኮልፌ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ለህብረተሰቡ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት በሚያስችል መልኩ የተገነባ መሆኑን አብራርተዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት እያስቀረ ያለ ውጤታማ ስራ ነው ብለዋል። በዚህም በመዲናዋ የመሶብ አንድ ማዕከላት ተደራሽነትን በማስፋትና የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን የመፈፀም ውጤታማነትን እያሻሻለ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ወልደ ሚካኤል፤ የኮልፌ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የክፍለ ከተማውን አገልግሎቶች ለማሳለጥ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ የግብርና ምርምር ቴክኖሎጂዎች ሽግግርን እያጠናከረ ነው
Jun 4, 2026 248
ሐረር፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ) ፡-የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የአየር ንብረት መለዋወጥን መቋቋም በሚችሉና ከፍተኛ ምርት በሚሰጡ የግብርና ምርቶች ላይ የሚያከናውነውን የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ይበልጥ እያጠናከረ መሆኑን አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዝዳንት ይስሃቅ ዩስፍ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር አብሮ የሚሄዱ የሰብል ዝርያዎችና የእንስሳት እርባታ ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። በተለይም በየአካባቢው የሚከሰተውን ተለዋዋጭ የአየር ንብረት ሁኔታ ተቋቁመው የተሻለ ምርት መስጠት የሚችሉ አዳዲስ የሰብልና የእንስሳት ዝርያዎችን ለህብረተሰቡና ለአርሶ አደሩ የማሰራጨት እንዲሁም የማስፋት ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዚህም መሰረት በዘንድሮው ዓመት ብቻ የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው ምርት መስጠት የሚችሉ 120 ነባርና አዳዲስ የግብርና ውጤቶችን ለማህበረሰቡ ማዳረስ መቻሉን ምክትል ፕሬዝዳንቱ አስታውቀዋል። ዩኒቨርሲቲው በግብርናው ዘርፍ ላይ ብቻ ሳይሆን በጤና እና ቴክኖሎጂዎች ላይም እየሰራና እውቅና እያገኘ እንደሚገኝም አክለዋል። በተለይም በቴክኖሎጂ ረገድ የአየር ንብረት ለውጥ ተስማሚና ወጪ ቆጣቢ፣ ምቹ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር የማፍለቅ ስራዎች እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዩኒቨርሲቲው የዕጽዋት ሳይንስ መምህርና የግብርና ምርምር ትኩረት መስክ አስተባባሪ ዮናስ ሞገስ(ዶ/ር)፤ የአየር ንብረት ለውጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና በምርትና ምርታማነት ላይ ተፅዕኖ እያስከተለ ይገኛል ብለዋል። በተለይም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ጎልቶ እንደሚስተዋል ጠቅሰው፤ ችግሩን ለመቅረፍ ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን መስራቱን ተናግረዋል። በዚህም ባለፈው ዓመት ድርቅን ተቋቁመው ምርት የሚሰጡ ሁለት የለውዝ ዝርያዎችን በምርምር በማውጣት ዝናብ አጠር አካባቢ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የማሰራጨት ስራ ማከናወኑን አንስተዋል። ሌሎች የአየር ንብረት ለውጥን ሊቋቋሙ የሚችሉ የተለያዩ የሰብል ዝርያዎች ላይም ምርምሮችን በማከናወን ለተጠቃሚው የማዳረስና የማስፋት ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው በቴክኖሎጂ ዘርፍም አዳዲስና የማህበረሰቡን ችግሮች የሚፈቱ የምርምር ስራዎችን እያወጣ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ማኔጂንግ ዳይሬክተር፣ መምህርና ተመራማሪ ኢንጅነር ሃምዛ አህመድኑር ናቸው። በተለይም በአካባቢው በሚገኙና ወጪ ቆጣቢ የሆኑ ቁሶችን ተጠቅሞ የመኖሪያ ቤት መገንባት የሚያስችል የምርምር ስራ ማከናወኑን የገለጹት ኢንጅነር ሃምዛ፤ ይህም እንደ ሀገር ተቀባይነት ማግኘቱንና የማስፋት ስራውም እየተከናወነ መሆኑን አክለዋል። የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ 43ኛው ዓመታዊ የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ግምገማ ጉባዔውን ሰሞኑን ማካሄዱ ይታወሳል።
ስፖርት
ወላይታ ድቻ እና ነገሌ አርሲ ነጥብ ተጋሩ
Jun 4, 2026 301
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ34ኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ እና ነገሌ አርሲ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የተካሄደው በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ነው። ውጤቱን ተከትሎ ወላይታ ድቻ በ44 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። ነገሌ አርሲ በ53 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ሊካሄድ የነበረው የወላይታ ድቻ እና የነገሌ አርሲ ጨዋታ፣ በወቅቱ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ወደ ዛሬ መዘዋወሩ የሚታወስ ነው።
የረቀቁ የአበረታች ቅመሞች አጠቃቀም ስልቶችን ለመከላከል የሚያስችል ተቋማዊ አቅም እየተገነባ ነው-ባለስልጣኑ
Jun 4, 2026 361
አዳማ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፦ የረቀቁ የአበረታች ቅመሞች አጠቃቀም እና የማጭበርበር ስልቶችን ለመግታት የሚያስችል ተቋማዊ አቅም እየተገነባ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መኮንን ይደርሳል ገለጹ። የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በስፖርት ውስጥ የተከለከሉ አበረታች ቅመሞች (Doping) እና ዘዴዎች አስመልክቶ ለስፖርት ጋዜጠኞች ያዘጋጀው የስልጠናና የውይይት መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩ ባለስልጣኑ የተከለከሉ አበረታች ቅመሞች (Doping) እና ዘዴዎች የሚፈጥሩትን አሉታዊ ተፅዕኖ የመከላከል እና የመቆጣጠር ስራ ይበልጥ ውጤታማ እና ተደራሽ ለማድረግ እያከናወነው ባለው ስራ የስፖርት ጋዜጠኞች ያላቸውን ሚና ማሳደግን ያለመ ነው። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መኮንን ይደርሳል የስፖርት ጋዜጠኞች በአበረታች ቅመሞች ዙሪያ የስፖርት ማህረሰቡን እና የባለድርሻ አካላትን ግንዛቤ በመፍጠር ውጤታማ ስራዎችን መስራት እንደሚችሉ ገልጸዋል። የፀረ አበረታች ቅመሞች ስራ ከሚዲያ ስራ ነጥሎ ማየት እንደማይቻል ጠቅሰው፥ በዚህ ረገድም ሚዲያ የማይተካ ሚና እንዳለው አመልክተዋል። በአበረታች ቅመሞች ዙሪያ ባለፉት ዓመታት ሚዲያው ተግቶ ሲሰራ መቆየቱንና የአመላካከት ለውጥ እየመጣ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ፀረ አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን ከነበረበት ችግር ወጥቶ ባለፉት ዓመታት ጠንካራ ተቋማዊ አቅም በመገንባት በአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ደረጃ ተምሳሌት መሆን መቻሉን ተናግረዋል። የፀረ አበረታች ቅመሞች ስራ የበለጠ በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እየታገዘ እንደሚገኝና ባለስልጣኑም ከወቅቱ ጋር በመራመድ ተቋማዊ ብቃቱንና የመፈጸም አቅሙን ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል። የአበረታች ቅመሞች በስርዓተ ትምህርት ውስጥ መካተትና በስፖርት እና የስልጠና ማዕከላት ተከታታይ ግንዛቤ መፍጠር ስራዎች እየተከናወኑ በመሆናቸው በዘላቂነት ውጤት እንደሚያመጡ ገልጸዋል። ባለስልጣኑ የምርምር እና የቁጥጥር አቅሙ መጨመሩን እያሳደገ እንደሚገኝና ህገ ወጥ ተግባር በሚፈጽሙ አትሌቶች እና ሌሎች አካላት ላይ የህግ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የምርምር እና ቁጥጥር ተሞክሮ እና ውጤቶች ማስፋት እና ማጠናከር እንደሚገባም ነው ዋና ዳይሬክተሩ የገለጹት። የፀረ አበረታች ቅመሞች የመከላከል እና የመቆጣጠር አቅም ማደግ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ተሳትፎ፣ተወዳዳሪነት እና ውጤታማነት ለማሳደግ እንደሚያስችል አመልክተዋል። በዓለም አቀፍ ውድድሮች ተሳትፎን ለማረጋገጥ የፀረ አበረታች ቅመሞች መመዘኛዎች ማሟላት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። የስፖርት ፍትሃዊነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ጠቅሰው፥ አትሌቶች ሙያ፣ ተፈጥሯዊ ጥረት እና አቅም በመጠቀም ውጤት ለማምጣት መስራት አለባቸው ብለዋል። የስፖርቱን ተአማኒነት ለማጽናት እና ለማስቀጠል የፀረ አበረታች ቅመሞች ስራ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አመልክተዋል። አትሌቶች እና ዜጎች ከጤና፣ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሌሎች ችግሮችና ቀውሶች ለመጠበቅ የቁጥጥርና የምርመራ ስራውን ማጠናከር ተገቢ እንደሆነም አንስተዋል። የአበረታች ቅመሞች አጠቃቀም በቴክኖሎጂ እና ሳይንስ ታግዘው እየረቀቁ መምጣታቸውን የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ ከጊዜው ጋር የሚሄድ ቀጣይነት ያለው ተቋማዊ አቅም ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። በዚህ ረገድም መገናኛ ብዙሃን የተከለከሉ አበረታች ቅመሞች መከላከል እና መቆጣጠር ላይ ያላቸውን ግንዛቤ መፍጠር እና የአመለካከት ለውጥ የማምጣት ስራ እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል። በውይይቱ ላይ ዶፒንግ ፤ የጋዜጠኞች ስነ ምግባር፤ የአበረታች ቅመሞች ፅንሰ ሀሳቦች፣ ዓለም አቀፍ የዶፒንግ ተጽእኖና የኢትዮጵያ ፀረ አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን እንቅስቃሴ በሚሉ ጉዳዮች ላይ የመወያያ ሰነዶች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው የወጣው መርሐ ግብር ያሳያል። የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በሀገራችን ስፖርት ውስጥ የተከለከሉ አበረታች ቅመሞች (Doping) እና ዘዴዎች የሚፈጥሩትን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 400/2009 ስልጣን ተሰጥቶት የተቋቋመ የፌዴራል ተቋም ሲሆን ባለፉት 8 ዓመታት በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል ህብረተሰቡንና የስፖርቱን ቤተሰብ በስፋት ለማንቃት የተጠናከሩ የሚዲያ ንቅናቄ ፕሮግራሞችን በተለያዩ የሚዲያ ተቋማትና የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ በስፋት ተግባራዊ ማድረግ ይገኝበታል።
የወላይታ ድቻ እና የነገሌ አርሲ የ34ኛ ሳምንት መርሐ ግብር
Jun 4, 2026 311
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፦ በዝናብ ምክንያት የተራዘመው የወላይታ ድቻ እና የነገሌ አርሲ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ34ኛ ሳምንት ጨዋታ ዛሬ ይካሄዳል። ጨዋታው ከቀኑ 9 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይከናወናል። ወላይታ ድቻ በሊጉ ካደረጋቸው 33 ጨዋታዎች መካከል በዘጠኙ ድል ሲቀናው ስምንት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ 16 ጨዋታዎች ላይ አቻ ተለያይቷል። በ33ቱ ጨዋታዎች ላይ 32 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 29 ግቦችን አስተናግዷል። ወላይታ ድቻ በ43 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚ ነገሌ አርሲ በበኩሉ 33 ጨዋታዎችን አድርጎ በ13ቱ ሲያሸንፍ በሰባቱ ተሸንፏል። 13 ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። 32 ግቦችን ሲያስቆጥር 25 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ነገሌ አርሲ በ52 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ወላይታ ድቻ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። ነገሌ አርሲም ካለፉት ሁለት ጨዋታዎች ሶስት ነጥብ ማግኘት አልቻለም። ጨዋታው ሁለቱ ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ሊካሄድ የነበረው የወላይታ ድቻ እና የነገሌ አርሲ ጨዋታ፣ በወቅቱ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ወደ ዛሬ መዛወሩ ይታወሳል።
አንዶኒ ኢራኦላ የሊቨርፑል አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
Jun 3, 2026 542
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦አንዶኒ ኢራኦላ እስከ ሰኔ 2028 (እ.አ.አ) የሚቆይ የሁለት አመት ውል በመፈረም አዲሱ የሊቨርፑል አሰልጣኝ ሆኗል። የቀድሞውን አሰልጣኝ አርነ ስሎትን በመተካት የሊቨርፑልን የአሰልጣኝነት መንበር የሚረከበው ኢራኦላ፤ በያዝነው ሳምንት ውስጥ በይፋ ለደጋፊዎችና ለሚዲያ እንደሚተዋወቅ የስፖርት ጋዜጠኛው ፋብሪዚዮ ሮማኖ ገልጿል። የ43 ዓመቱ አሰልጣኝ ቦርንማውዝን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በሊጉ 6ኛ ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅ በማድረግ ለዩሮፓ ሊግ ተሳትፎ ማብቃት ችሏል። አሰልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላ ከእሱ ጋር አብረው የሚሰሩትን ፓብሎ ዴ ላ ቶሬ፣ ቶሚ ኤልፊክ፣ ሻውን ኩፐር እና ቶም ዌበርን ያካተተ የአሰልጣኞች ቡድን ወደ አንፊልድ ይዞ እንደሚመጣ ይጠበቃል።
አካባቢ ጥበቃ
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ
Jun 3, 2026 602
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዮት አስታወቀ። የኢትዮጵያ የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል። እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል። የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል። በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል። በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ይሆናል። በመደበኛ ሁኔታ ወቅታዊው የክረምት ዝናብ ቀደም ብሎ በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ አጋማሽ የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚጀምር ሲሆን፤ በሂደት እየተጠናከረ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ አካባቢዎች እንደሚስፋፋም ገልጿል። በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛውና በምስራቅ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ዝናቡ በመጠንም ሆነ በስርጭት የተሻለ እንደሚሆን ይጠበቃል ብሏል። የሚኖረው እርጥበት ለግብርና ስራ የማሳ ዝግጅት እና የመኸር ሰብሎችን ለመዝራት እንዲሁም ለበልግ ሰብል ተጠቃሚ አካባቢዎች መልካም አጋጣሚ እንደሚኖረው ጠቁሟል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የአገሪቱ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው የገጽምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው ይጠበቃል ብሏል። በዚህም በመካከለኛው እና ታችኛው አባይ፣ ላይኛው እና መካከለኛ ባሮ አኮቦ፣ ላይኛው ስምጥ ሸለቆ፣ ኦሞ ጊቤ፣ አዋሽ እንዲሁም ገናሌ ዳዋ ከመካከለኛ እስከ ከባድ የገጸ ምድር ውሃ ፍሰት ይኖራቸዋል ብሏል። በላይኛው አባይ፣ ኦጋዴን፣ መካከለኛው አዋሽ፣ ስምጥ ሸለቆ እና ኦሞ ጊቤ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገጸ ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸውም ገልጿል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማ ማህበረሰብን ለመፍጠር ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው
Jun 3, 2026 513
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረጉት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጤናማ ማህበረሰብን ከመፍጠር አኳያ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የኢትዮጵያ አካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሸጋው ፈንታዬ ገለጹ። ማህበሩ እነዚህን ስራዎች የሚደግፉ የምርምር፣ የአቅም ግንባታና ሌሎች ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ምቹ የአየር ፀባይ ሁኔታ እና ንጹህ አካባቢዎችን ለማስፋፋት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ፣ በጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄና ሌሎች መርሃ ግብሮች በተከናወኑ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ ነው። የኢትዮጵያ አካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሸጋው ፈንታዬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ጤናማ ማኅበረሰብን ለመፍጠር ለዜጎች ተስማሚ የሆነ የመኖሪያ አካባቢን መፍጠር ይጠይቃል። የደኖች ጭፍጨፋ እንዲሁም የአካባቢን ንጽህና አለመጠበቅ የዜጎች ጤና ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር አንስተዋል። በኢትዮጵያ ላለፉት ዓመታት ተግባራዊ የተደረጉት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እንዲሁም የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ስራዎች የአካባቢ ጤናን በመጠበቅ ለማኅበረሰብ ጤና ጉልህ አስተዋጽኦ አላቸው ብለዋል። የአካባቢን ንጽህና መጠበቅ ዜጎችን ከተለያዩ በሽታዎች እንደሚጠብቅም አክለዋል። የኢትዮጵያ አካባቢ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማኅበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ስራዎች ላይ ገንቢ ሚና በመጫወት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ማህበሩ እነዚህን ስራዎች የሚደግፉ የምርምር፣ የአቅም ግንባታና ሌሎች ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር አለማየሁ ሀዲስ በበኩላቸው፤ የአየር ንብረት ለውጥ መዛባት እና የአካባቢ ንጽህናን አለመጠበቅ በዜጎች ጤና ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ለመከላከል የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን እና አካባቢን ንጹህ ለማድረግ የሚሰሩ ተግባራትን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራን የአካባቢን ጤና ለመጠበቅ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን ሊያጠናክሩ ይገባል ብለዋል።
በሐረሪ ክልል ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል
May 28, 2026 2726
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን የክልሉ የግብርና ልማት ቢሮ አስታውቋል። የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ነስረዲን አህመድ እንደገለጹት በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ይተከላሉ። ከሚተከሉ ችግኞች ውስጥም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የፍራፍሬና የደን ችግኞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም ከ200 ሺህ በላይ የሚሆኑት ለእንስሳት መኖ የሚያገለግሉ ችግኞች መሆናቸውንም ገልጸዋል። በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ የችግኝ ጣቢያዎች እየተከናወነ በሚገኘው ስራም ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን አንስተዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር እስከ አሁን የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት የክልሉን የደን ሽፋን በማሳደግና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሻሻሉ መምጣታቸውንም ነው የተናገሩት።
የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር ያወጣቸውን ችግኞች ለአርሶ አደሩ እያሰራጨ ነው
May 28, 2026 1567
ሚዛን አማን፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር ያወጣቸውን የቡና፣ የቅመማቅመም እና የፍራፍሬ ችግኞች ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑን ገለጸ። ማዕከሉ በገበያ ተፈላጊ የሆኑ የካካዎ፣ የቫኔላና ሌሎች የቅመማቅመም ችግኞችን ለመጪው ክረምት ተከላ ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑን አስታውቋል። የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ደረጀ ቱሉ (ደ/ር) እንዳሉት፣ ማዕከሉ የአርሶ አደሩን ምርታማነት የሚያሻሽሉና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ ከ70ዐ ሺህ በላይ የቅመማቅመም ችግኞችን እያዘጋጀ ይገኛል። ችግኞቹ በመጪው ክረምት የሚተከሉ ሲሆን ለአካባቢ ሥነ ምህዳር ተስማሚና ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በክረምቱ የሚተከሉ ችግኞች ምርታማነታቸው ከፍ ያለ ከመሆኑ በላይ የአካባቢው ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ ተደማሪ አቅም እንደሚሆኑም አስረድተዋል። የሸካ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ምክትል ኃላፊ አለምሰገድ ኃይለኢየሱስ በበኩላቸው ማዕከሉ ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ የቅመማቅመምና ሌሎች ችግኞችን ለአርሶ አደሩ ማቅረቡን ተናግረዋል። በዚህም የአርሶ አደሩን ምርታማነት በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ እንደቻለ አክለዋል። ተግባሩን በማስቀጠልም ማዕከሉ በበጋ ወራት ያፈላቸውን ችግኞች ለክረምቱ ወቅት ተከላ ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑንም ገልጸዋል። በዞኑ የየኪ ወረዳ አርሶ አደር መሐመድ ታዬ እና አርሶ አደር አየለች አናሞ በበኩላቸው ከምርምር ማዕከሉ የሚቀርቡ ዝርያዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጡና ምርታማነታቸው ያደገ መሆኑን በተግባር ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል። ዘንድሮ በራሳቸው ያዘጋጁትንና በማዕከሉ የተዘጋጁ ችግኞችን በመትከል ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ወደ ሥራ መግባታችውን አመልክተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 3698
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 4458
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 3294
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 3201
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 24, 2026 3804
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የመደመር ማሳያ ከሳምንቱ አበይት ክስተቶች መካከል የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች በአሶሳ ከተማ ያስገነቡት የጋራ ሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህንፃ ምረቃ ይጠቀሳል። በክልሎቹ ትብብር የተከናወነው የህንፃ ግንባታ በመደመር እሳቤ የዜጎችን የጋራ ሰላም ለማስጠበቅና የልማት ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ ጥረት ማሳያ ነው። መርሃ ግብሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) የተገኙበት ነበር። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም ላይ ያተኮረው መድረክ በሶማሌ ክልል ጂግጂጋ ከተማ የተካሄደውና በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ ያተኮረው ፎረምም በእዚህ ሳምንት ዐበይት ጉዳይ ነበር። ፎረሙ የተካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን የተዘጋጀውም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ጠቅሰዋል። እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልጽነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑም በቀጣናው ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ ነው ያነሱት። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ምሁራን ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ እንዲያስቀምጡም ያግዛል ብለዋል። የጉባ ላይ ብስራቶች ተግባራዊ ልማት የሳምንቱ የበረራ ቅኝታችን የሚጀምረው ወደ ሶማሌ ክልል ጎዴ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በስፍራው እየተገነባ ያለውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላም በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት የመሬት፣ ውሃ እና የሚያለማ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በቂ ሃብት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህን ካሟላን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ማድረግ ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የኒውክለር ሃይል ማመንጫ፣ የቢሾፍቱ አየር መንገድ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የቤቶች ልማት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጓቸው የጉባ ብስራቶች መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀው ስራ ያስጀምሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በግራንዴር ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተገነባው ፋብሪካ፣ መሰረት ልማቱ በ300 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ፣ የዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የሴራሚክና የፎርሲሌን ንጣፎች ማምረቻ ፋብሪካ ነው። የፋብሪካው መገንባት የውጭ ምርት ጥገኝነት ከመቀነስ ባለፈ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑ ታውቋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ ጉብኝት በዚሁ ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ወደ ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጓዝ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በድሬዳዋ ቆይታቸው ብርቱካንና ሌሎች የፍራፍሬ ልማት ሥራዎች እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ልማት ስራን ተመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የግብርና ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባስተላለፉት መልእክትም የጋራ ሙለታ ተፈጥሯዊ የልማት ፀጋና ከፍታም ታሪክን፣ ውብ መልክዓ ተፈጥሮን የታደለ፣ የኢትዮጵያን ሜዳና ተራሮች ምርት የሚታፈስባቸው የማድረግ ሀገራዊ ጉዞ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ማሳያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ ተገኝተው 142 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ ያስጀመሩትም በዚህ ሳምንት ነበር። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በለውጡ ዓመታት ከልማት የራቁ አካባቢዎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ መሰራቱን አንስተዋል። የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የንጽህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶች ለዚሁ ማሳያ ናቸው ብለዋል። በተመሳሳይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ እና የመስኖ ፕሮጀክቶች መርቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በተለይ አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልት የሚያስቀር ነው። የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። በሲዳማ ክልልም በፌደራል መንግስት ድጋፍ በ460 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታም ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 75 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ነው። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከ543 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 52 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መመረቃቸው ሌላው የሳምንቱ ክስተት ነበር። በዞኑ ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትንም መርቀዋል። ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግበት የሃዋሳ ከተማ ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም በዚህ ሳምንት ተካሂዳል። ለፕሮጀክቱ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ የፕሮጀክቱ ግንበታ ሲጠናቀቀ ሀዋሳ ከተማዋን ጽዱ በማድረግ የቱሪዝምና የኢንቨስመንት ማዕከልነቷን ያሳድገዋል ተብሏል። አቶ ደስታ የፕሮጀክቱ ግንባታ መንግስት ለከተሞች እድገት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉም ነው የጠቀሱት። የከሰም መስኖ ግድብ የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክትም በዚሁ ሳምንት ተመርቆ ሥራ ጀመሯል። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ነው። የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ያስቀራል ተብሏል። በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብርሃም (ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር። የጥገና ማሻሻያው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን ይህን የአደጋ ስጋት በማስቀረት ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል የሚያስችል ነው። ለፕሮጀክቱም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ሚኒስትሩ አንስተዋል። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል። የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የሀዝቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም አንስተዋል። የግንቦት - ታላቁ ሁነት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ሂደቱን ስኬታማ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አጠቃላይ ዜጎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በዚሁ ሳምንት "ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የመገናኛ ብዙሃን ሚ ና" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአዳማ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎና የዳበረ የዴሞክራሲ ልምምድ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅም መገናኛ ብዙሃን የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ከተረጅነት የመውጣት ሀገራዊ ጥረት በድሬዳዋ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረክም ሌላው የእዚህ ሳምንት ዓቢይ ጉዳይ ነው። መድረኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የግብርና ሚኒስቴር በመተባበር ያዘጋጁት ነው። በመድረኩም በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተነስቷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቂና የተሟላ የውሃ ሀብት፣ የተማረና አምራች የሆነ ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም ለም የመሬት ፀጋዎች ያሉባት ሀገር በመሆኗ በማልማት እድገትና ማንሳራራትን ማስቀጠል ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። ለእዚህም ዋናው መሠረታዊ ጉዳይም ያሉ አቅሞችን በመለየትና ህዝብን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ በማሸጋገር በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጡን ሥራ በላቀ ደረጃ ማስቀጠል መቻል መሆኑን አንስተዋል። ለሰላም ጥሪ የተሰጠ ምላሽ የሠላም ጥሪን የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም (ዲዲአር) መርሀግብርም በዚህ ሳምንት ተከናውኗል። በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል ጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ ሆነው የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ታጣቂዎቹ ሠላምን አማራጭ በማድረግና የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፣ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል። በተመሳሳይ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የክልሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮምቦልቻ የስልጠና ማዕከል ስልጠና የጀመሩ መሆኑ ይታወቃል። ሐረር- ፕሮጀክቶች ምረቃ የሐረሪ ክለል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙትን የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝትም ሌላው የእዚህ ሳምንት ኩነት ነበር። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተሻለ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ። በተለይም የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መገንባት የክልሉን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የበለጠ በማሳደግ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት። በዘመናዊ ትምህርት የታነፀና በእውቀት የበለፀገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማፍራት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቶቹ በፍጥነትና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ለማስቻል በአስተዳደሩ በኩል ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት 672 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በይፋ የተመረቀውም በዚህ ሳምንት ነው። በምረቃው ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን፣ የክልሉ የመንገዶች ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢድሪስ ሙሴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እንደገለጹት ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የከተማውን የንግድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያስችል ነው። የከተማውን ገፅታ በመለወጥ ረገድም የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ነው ያነሱት። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገድ ፕሮጀክቱ የጂግጂጋ ከተማን ልማትና ዕድገት በማፋጠን በኩል ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን አስተዳደሩ ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ዕቅድን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 30 ሜትር ስፋት እንዳለውም ታውቋል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 3540
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 3772
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 3574
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
ትንታኔዎች
በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ …
Jun 3, 2026 913
በዮሐንስ ደርበው በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር ሞላወርቅ አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በዓለምም ሆነ በሀገራችን አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው የደም ግፊት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በቆይታቸውም፤ ለደም ግፊት አጋላጭ ስለሆኑ ምክንያቶችና ሊደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄም እንዲሁም ከመድሃኒት አወሳሰድ ጋር በተያያዘ ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን አቅርበዋል። · የደም ግፊት ምንድን ነው? ደም በደም ሥሮቻችን ሲያልፍ፤ የሚለካው መጠን “የደም ግፊት” እንደሚባል ዶክተር ሞላወርቅ ያስረዳሉ። የላይኛው (ሲስቶሊክ ወይም ከፍተኛው) የደም ግፊት መጠን ልብ በምትኮማተርበት ጊዜ ደም ወደ ደም ሥር ሲረጭ የሚለካው መሆኑንም ይገልጻሉ። የታችኛው (ዲያስቶሊክ ወይም ዝቅተኛው) የደም ግፊት መጠን ደግሞ ልብ ደም ለመቀበል ለአፍታ ዕረፍት በምታገኝበት ጊዜ የሚከሰት የግፊት ደረጃ መሆኑንም ይገልጻሉ። · የደም ግፊት ደረጃዎች እና ማስጠንቀቂያቸው ዶክተር ሞላወርቅ እንደሚሉት፤ የጤናማ ሰው የደም የግፊት መጠን 120 በ 80 እና በታች መሆን ይኖርበታል። በሌላ በኩል ግን ይላሉ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 የታችኛው ደግሞ ከ80 በታች ከሆነ “ከፍ ያለ ወይም የጨመረ የደም ግፊት ደረጃ” ይባላል። የላይኛው ከ130 እስከ 139 ወይም የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከሆነ ደግሞ “ደረጃ አንድ የደም ግፊት” እንደሚባል ያስረዳሉ። የላይኛው ከ140 በላይ ሲሆን እና የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ ደግሞ “ደረጃ ሁለት የደም ግፊት” እንደሚባል ነው የሚገልጹት። በሌላ በኩል “የከፋ የደም ግፊት ደረጃ” የሚባል እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም የላይኛው ከ180 በላይ እና የታችኛው ከ120 በላይ ሲሆን ነው በማለት ያብራራሉ። · ለደም ግፊት መጨመር መንስዔዎቹ ምንድን ናቸው? በዋናነት ሁለት ዓይነት የደም ግፊት መኖሩን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ ከፍተኛ የደም ግፊት እና መንስዔው የሚታወቅ የደም ግፊት መሆኑን አስረድተዋል። በዋናነት ወይም በአብዛኛው ከ90 እስከ 95 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ ደም ግፊት የሚባለው መሆኑን ገልጸው፤ በርካታ መንስዔዎች ሊኖሩት እንደሚችሉ ቢገመትም ሁሉም በውል እንደማይታወቁ ያነሳሉ። ከበርካታ መንስዔዎቹ መካከልም፤ በቤተሰብ የሚወረስ (ተላላፊ)፣ አካባቢያዊ ምክንያቶች እንዲሁም የአኗኗር ዘይቤ የሚሉት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። የአኗኗር ዘይቤ ሲባልም፤ የአመጋገብ ሥርዓት በተለይም ጨው የበዛበት ምግብ፣ ክብደት መጨመር፣ አካባቢያዊ ሁኔታዎች (አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ)፣ የስኳር ታማሚ መሆን የሚሉት ይጠቀሳሉ ይላሉ። · ለደም ግፊት በተለይም እነማን ተጋላጭ ናቸው? ዕድሜ በጨመረ ቁጥር የደም ግፊት የመከሰት ዕድሉም እንደሚጨምር ጠቅሰው፤ በዚህም መሠረት ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ተጋላጭ መሆናቸውን ይናገራሉ። እንዲም በቤተሰብ የደም ግፊት ኬዝ ያለባቸው ሰዎች፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒክ ግሩፕ) ለምሳሌ፡- በጥቁሮች (አፍሪካውያን)፣ በኤስያውያን፣ በደቡብ ኤስያውያን ላይ ከፍተኛ የደም ግፊት ሊከሰት እንደሚችል ይገልጻሉ። እንደ ዶክተር ሞላወርቅ ማብራሪያ፤ በአጠቃላይ አጋላጭ ምክንያቶች በሁለት ተከፍለው ሊታዩ ይችላሉ። አንደኛው፡- ልንከላከላቸው (ልንቀንሳቸው) የምንችላቸው መሆናቸውን በመግለጽ ይህም የአመጋገብ ሥርዓትን ማስተካከል፣ ክብደት መቀነስ፣ አልኮልና ሲጋራ ማቆም እና መሰል መሆናቸውን አብራርተዋል። ሁለተኛው፡- ልንከላከላቸው የማንችላቸው መሆናቸውን ገልጸው ይህም፤ የዕድሜ መጨመር፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒሲቲ) እና በቤተሰብ የሚተላለፍ የሚሉትን ጠቅሰዋል። · የደም ግፊትን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? የደም ግፊ ከተከሰተ መቆጣጠር እንጅ ማዳን እንደማይቻል ገልጸው፤ ከላይ እንደተጠቀሰው አስቀድሞ መከላከል ወይም ማዘግየት የሚቻል እና መከላከል የማይቻል የደም ግፊት ደረጃ መኖሩን አስረድተዋል። · የደም ግፊት በውል የሚታወቅ ምልክት አለው? የደም ግፊት ሲከሰት ምልክት እንደሌለው በማንሳት፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ “ዝምተኛው ገዳይ” እስከመባል መድረሱን ዶክተር ሞላወርቅ ያነሳሉ። ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ግን፤ በአንድ ወይም በሁለት የሰውነት አካል ላይ ችግር ሊደርስ እንደሚችል ከዚህም ሲያልፍ እስከ ሞት እንደሚያደርስ ይጠቅሳሉ። በተያያዘም፤ የራስ ምታት፣ የዐይን ብዥ ብዥ ማለት፣ ትንፋሽ ማጠር፣ የድካም ስሜት፣ አንገት የመያዝ ዓይነት ስሜቶች የደም ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ሊስተዋሉ የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል። አክለውም፤ በአብዛኛው በሕብረተሰቡ ላይ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከፍተኛ ደረጃ ይደርስና ድንገት በጨመረ ጊዜ፤ ለሞት፣ ለአደጋ፣ ለልብ ድካም፣ አጣዳፊ ለሆነ የልብ ህመም፣ በጭንቅላት ላይ የደም መፍሰስ፣ የኩላሊት ድክመት፣ በደም ሥሮች በአግባቡ ደም እንዳይተላለፍ ማድረግ፣ ለዐይነ ስውርነት መዳረግን ጨምሮ መሰል ጉዳቶችን ሊያስከትል እንደሚችል አስገንዝበዋል። · መድኃኒት አወሳሰድ ላይ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ ዶክተር ሞላወርቅ እንደገለጹት፤ አንድ ሰው ደም ግፊት እንዳለበት ከተነገረው በኋላ ሕክምናውም እንደ ደም ግፊቱ ደረጃ ይለያያል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 ከሆነ “የጨመረ ግፊት” ይባላል፤ እዚህ ላይ ሰውየው ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ አመጋገቡን እንዲያስተካክል፣ ስፖርት እንዲሠራ፣ ክብደት እንዲቀንስ፣ ሱስ (ሲጋራ፣ አልኮል) እንዲቀንስ ክትትል ይደረጋል ብለዋል። ስለዚህ መድኃኒት ሳይጀምር የአኗኗር ዘይቤን በማስተካከል የደም ግፊቱን ሊቀንሰው (ሊቆጣጠረው) ይችላል ማለት ነው ሲሉም ይገልጻሉ። “ደረጃ አንድ ግፊት” የሚለው ላይ ከደረሱ ግን ሕክምና የሚጀምሩም የማይጀምሩም እንዳሉ ተናግረዋል። ይህም ማለት የላይኛው ከ130 እስከ 139 የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከደረሰ ሕክምና የሚጀምሩት የስኳር ህመም ያለባቸው፣ የስትሮክ ህመም ያለባቸው፣ ከልብና ደም ሥር የተገናኙ ህመሞች ያሉባቸው ከሆኑ ቢያንስ አንድ የግፊት መድኃኒት መጀመርና ክትትል ማድረግ አለባቸው ይላሉ። በሌላ በኩል ግን ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ ሰዎች “ደረጃ ሁለት ግፊት” ላይ ከደረሱ (የላይኛው ከ140 የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ) ሁሉም መድኃኒት መጀመር እንዳለባቸው በአጽንዖት ገልጸዋል። የሚጀምሩት መድኃኒትም አሁን ባለው በተሻሻለው የሕክምና ዘይቤ ሁለት መድኃኒቶች የሚጀምሩበት ሁኔታ እንዳለ ነው የሚያስረዱት። የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል ግን ለሁሉም የግፊት ዓይነቶች መሠረት (የሚመከር) መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ መድኃኒት ጀምሬያለሁ ብሎ የአኗኗር ዘይቤው ላይ ቸልተኝነት ሊኖር እንደማይገባም ነው የሚመከሩት። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከግፊት ጋር በተያያዘ ወደ ሆስፒታል መጥተው የሚታከሙ ታካሚዎች አብዛኞቹ፤ ጀምረው ያቋረጡ፣ ለመጀመር ፍላጎት የሌላቸው፣ ቅድመ ምርመራ ባለማድረግ ምክንያት ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ የተጎዱ ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። ስለዚህ የግፊት መድኃኒት ከተጀመረ ሊቋረጥ እንደማይችል አስጠንቅቀዋል። በየጊዜው ክትትል ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በሂደት እንደ ግፊቱ ሁኔታ መድኃኒቶች ሊቀነሱም ሊጨመሩም እንደሚችሉ አመላክተዋል። · የመስፋፋት ደረጃ የዓለም ጤና ድርጅት በ2024 ያወጣውን መረጃ ዋቢ አድርገው፤ 1/3ኛው የዓለም ሕዝቦች በደም ግፊት እንደሚጠቁ ዶክተር ሞላወርቅ አንስተዋል። ከእነዚህ መካከልም፤ 7 ነጥብ 6 ሚሊየን ገደማው በአንድም በሌላም ምክንያት ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ጠቁመዋል። አብዛኞቹ የደም ግፊት ታማሚዎች ቁጥር የሚመዘገበው ደግሞ በመካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ሀገራችንን ያካትታል ሲሉ ገልጸዋል። በሀገራችን ደረጃም ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ባይኖሩም ከግፊት ጋር በተያያዘ በ2001 ላይ በ35 ሳይቶች የተጠኑ ጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከ21 እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ በደም ግፊት የሚጠቃ ነው ይላሉ። በአብዛኛው ደግሞ ከተማ ላይ እንደሚበዛ ጠቁመው፤ በተለይም አዲስ አበባ ላይ እስከ 30 በመቶ እንደሚደርስ የጥናቶቹ ውጤቶች ማመላከታቸውን ተናግረዋል። አብዛኞቹ ኬዞች ደግሞ ዕድሜያቸው ከፍ ያለ፣ ክብደታቸው የጨመረ፣ አልኮል እና ሲጋራ የሚጠቀሙ እና የስኳር ህመም ያለባቸው ሰዎች ጋር የሚገናኙ መሆናቸውን አስረድተዋል። እንደ ዓለም አቀፍ ደረጃም ኬዙ ካለባቸው መካከል ግማሽ ያህሉ ግፊት እንዳለባቸው እንኳን እንደማያውቁ ነው የሚገልጹት። ለግፊት ሕክምና ትክክለኛ ክትትል አድርገው ግፊታቸውን በአግባቡ የሚቆጣጠሩት ከ 5 ሰዎች 1 መሆኑንም ጥናቶች ያሳያሉ ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ በሀገራችን በሕብረተሰቡ ዘንድ ለደም ግፊት መለካት ኬዙ ከተገኘም የሕክምና ክትትል የማድረግ ሁኔታዎች ዝቅተኛ መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ሕብረተሰቡ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከአካል ጉዳት እስከ ሞት ሊያደርስ እንደሚችል ተገንዝቦ፤ የደም ግፊቱን የመለካት ልምምዱን ሊያዳብር እንደሚገባ ዶክተር ሞላወርቅ መክረዋል። በሌላ በኩል እንደ ሀገራችን ባሉ ሆስፒታሎች በጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ ወይም መቋረጥ (ስትሮክ) ካለባቸው ሰዎች ከ70 እስከ 85 በመቶው ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ የሚከሰት መሆኑን ገልጸው፤ ድንገተኛ ግፊት መጨመር ከልብ እና ከደም ሥሮች ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዓለምም ሆነ እንደ ሀገር አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንደኛው ግፊት መሆኑንም አረጋግጠዋል። ስለዚህ የደም ግፊትን መለካት፣ የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል፣ ከሱስ መራቅ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር ለጤናማ ሕይወት ከፍተኛ ሚና እንዳለው መክረዋል።
ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት
May 24, 2026 4519
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኝ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአንጀት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች በውል ይታወቃሉ? ቀድሞስ መከላከል ይቻላል? የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። ለምን ቢሉ? ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ስላለው ይሆናል መልሱ። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫዎት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁንእንጅ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል።ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚህ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዐለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዐለም ዐቀፍ፣ አኅጉር ዐቀፍ እና ሀገር ዐቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ይህም ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫዎታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል። #የኮሪደር_ልማት #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 2268
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት
May 17, 2026 5817
በኢዜአ ዐይን …! በዮሐንስ ደርበው እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉን የሚሉ እሮሮዎች በተለያዩ ሕዝባዊ ውይይቶች ሲነሱ ቆይተዋል። በተለይም በአንዳንድ ተቋማት መንግሥታዊ አገልግሎት ለማግኘት እዚያም እዚህም መንከራተት፤ደግሞም ወረፋ በመጠበቅ መጉላላት ብሎም ለጊዜና ገንዘብ ወጪ መዳረግ ይስተዋላል የሚሉ ሐሳቦች ተስተጋብተዋል። ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ባሳለፍነው ሳምንት … መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል አሠራር በመንደፍ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ አስጀመረ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማዕከሉ አገልግሎት ባስጀመሩበት ወቅትም ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው ብለው ነበር። አሁን ላይም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋ ነው።መስፋፋቱም በማዕከላት ብዛት፣በአገልግሎት መስጫ መስኮቶች ቁጥር እና በአገልግሎት ዐይነቶች እየተገለጠ ነው። በዚህም በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት የተደራጁ ሲሆን ይህ አሃዝም ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት እና ያለውን ፈጣን እድገት ያመላክታል። ጉዳዩ የዜጎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ማላቅ፤ ብልሹ አሠራርንም መቅረፍ ነውና መንግሥት በልዩ ትኩረት ይዞታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ አሥተዳደርና በሐረሪ ክልል ጉብኝት ባደረጉበት ወቅትም፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የምልከታቸው አካል ማድረጋቸው ለጉዳዩ የተሰጠውን ከፍያለ ትኩረት ያሳያል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሶብ የሞባይል አገልግሎትን በመረቁበት ወቅት ደግሞ፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ብለዋል። አክለውም፤በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች ዕርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል፤ ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፤ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ መሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል ማለቱም ይታወቃል። የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አንተነህ ማሞ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ደግሞ፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር የተገልጋዮችን እርካታ ማረጋገጥ ያስቻለ ስኬት ተገኝቷል ብለዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጡ የመንግሥት አገልግሎቶችም ዜጋ ተኮር፣ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍልና የተገልጋዮችን ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ መሆናቸውን አብራርተዋል። በዲጂታል 2030 የአገልግሎት አሰጣጥ አመላካች ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚጠቀሱ 50 ሀገራት መካከል አንዷ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ዜጎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በኦንላይን በየትኛውም ቦታ ሁሉንም አገልግሎቶች እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ ስለመሆኑም እንዲሁ። አገልገሎቱን ያገኙ አስተያየት ሰጭዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ እንግልትን ያስቀረ፣ ጊዜና ወጭን የቀነሰ ነውና ይስፋፋ፤ ተጠናክሮም ይቀጥል። #መሶብ_የአንድ_ማዕከል_አገልግሎት #የዜጎችን_እንግልትና_ብልሹአሠራርን_መቅረፍ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #በኢዜአ_ዐይን
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 10668
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 6091
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 11864
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 10342
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 5047
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 4033
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።