ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የኢትዮጵያ ዕድገት አይቀሬ መሆኑን አመላካች አፈጻጸሞች ተመዝግበዋል
Oct 24, 2025 84
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡- በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ አፈጻጸሞች ስኬታማነት የኢትዮጵያን ብልጽግና አይቀሬነት አመላካች መሆናቸውን ሚኒስትሮች ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ ከሚኒስትሮች ጋር በመሆን በኮይሻ ግድብ አካሂደዋል። ከግምገማው ጎን ለጎንም ኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን ጨምሮ ጨበራ ጩርጩራ የዝሆኖች ዳና ሎጂን ጎብኝተዋል።   በዚሁ ወቅት የሥራና ክኅሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በሰጡት አስተያየት፤ መሪነት ያለንን ዐውቀንና ፀጋችንን ለይተን ወደ ሀብትነት መቀየርን ይፈልጋል ብለዋል። ከዚህ አንጻር ጨበራ ጩርጩራን በማልማት ወደ ሀብትነት የመቀየር ሥራ መሠራቱን ጠቅሰው፤ ይህም አካባቢውን በማስተሳሰር እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል ሲሉ ገልጸዋል። ከፍ ሲልም በቱሪዝሙ ዘርፍ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት አመላክተው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመሪነት ጥበብን ተጠቅመው ካለን በመጀመር መርኅ እየሠሩ መሆናቸውን ያሳያል ነው ያሉት።   ከ100 ቀናት አፈጻጸም ጋር በተያያዘ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በሰጡት አስተያየት ደግሞ፤ በሁሉም መስኮች ተስፋ የሚፈነጥቁ አፈጻጸሞች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። የግብርናው ዕድገት ከሌሎች ዘርፎች ዕድገት ጋር ተሳስሮ በመሠራቱ ተስፋችንን መጨበጥ ጀምረናል ብለዋል። የሕዳሴው ግድብ፣ የወልመል መስኖ፣ የማዳበሪ ፋብሪካ እና ሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶች ተስፋችንን መጨበጥ መጀመራችንን ብሎም የኢትዮጵያ ብልጽግና አይቀሬነት አመላካች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል። አፈጻጸሙ እንደሚያስረዳው የተቀመጡ ግቦች በስኬት እየተከናወኑ ነው፤ የግብርናው ዕድገትም በአርሶና አርብቶ አደሩ ኑሮ ሁሉ የሚገለጥ ሆኗል ነው ያሉት። የተመዘገቡት ውጤቶች የተገኙት በፈተና ውስጥ መሆኑ ደግሞ ሀገራችንን ፈተና ሳይበግራት ስኬታማ ጉዞ ማድረግ መቻሏን እንደሚያሳይ አንስተዋል። አዲስ የሥራ ባህል እየተፈጠረ መሆኑን ዐይቻለሁ ያሉት ሚኒስትሩ፤ ሕዝብን በማሳተፍ ጀምሮ የመጨረስ ዐቅም እያደገ መምጣቱንም ታዝቤያለሁ ብለዋል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ስለኮይሻ እና ጨበራ ጩርጩራ በሰጡት ሐሳብ፤ ካለፈው ዓመት አንጻር ሥራው እያደገ መሆኑን ተመልክቻለሁ ነው ያሉት። አዳዲስ መዳረሻዎች ተገንብተው ለኢኮኖሚ ማመንጨት ተደማሪ ዐቅም እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ የነበራትን ፀጋ ለይቶ እና ዐውቆ ወደ ሀብት መቀየር ጊዜ ይፈልግ ነበር፤ አሁን ጊዜው ሆኖ ወደ ሀብት እንዲቀየሩ እየተደረገ ነው ሲሉም አመላክተዋል። አሁን ላይ የቱሪዝም ሀብት እየሰፋ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በግንባታ ላይ የሚገኙት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ የሰው ልጅ ሊጎበኛቸው የሚገባ መዳረሻዎች እንደሚሆኑም ተናግረዋል። ሀገር ያላትን ዐቅምና ፀጋ በመለየት እየተከናወኑ ባሉ አዳዲስ መዳረሻዎች እና በ100 ቀናት አፈጻጸም በሁሉም ዘርፍ ለተገኙ ስኬቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ሚኒስትሮቹ ገልጸዋል።
በማክሮ ኢኮኖሚውና ኢኮኖሚያዊ ዕድገቱ የተገኘው ስኬት የሦስት ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው - አቶ አደም ፋራህ
Oct 24, 2025 83
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡- በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ከ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም እና የኢኮኖሚ ዕድገት አዝማሚያዎች ጋር በተያያዘ የተገኘው ስኬት የሦስት ቁልፍ ጉዳዮች ድምር ውጤት መሆኑን አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ ከሚኒስትሮች ጋር በመሆን በኮይሻ ግድብ አካሂደዋል። ከግምገማው በኋላም አቶ አደም ፋራህ ከ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም እና የኢኮኖሚ ዕድገት አዝማሚያዎች ጋር በተያያዘ አስተያየት ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በጂኦ ፖለቲካ ውጥረት፣ በኢ-ተገማች የታሪፍ ዲፕሎማሲ፣ በአቅርቦት ሰንሰለት መቆራረጥ ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚ ዕድገት መቀዛቀዝ ብሎም የተዳከመ ማክሮ ኢኮኖሚ ዐውድ በሚታይበት ሁኔታ በሀገራችን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስቀጠል ችለናል ብለዋል።   ለዚህ አመርቂ ውጤት ያበቃን የሦስት ዋና ዋና ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው ብዬ አምናለሁ ሲሉም ገልጸዋል። የመጀመሪያው ከለውጡ ወዲህ የዕይታ ለውጥ(ፓራዳይም ሽፍት) ማምጣት መቻላችን ነው ብለዋል አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያያት። ለስኬታችን ሁለተኛው ምክንያት የአመራሩ የማስፈጸም ዐቅም፣ ትጋትና ቁርጠኝነት መሆኑንም ጠቅሰዋል። እንዲሁም ሦስተኛው የሕዝቡ፣ የግሉ ሴክተር፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ እና ትብብር ማደግ መሆኑን አንስተዋል። መንግሥት ሕዝቡ በተደጋጋሚ ሲያነሳቸው የነበሩትን፤ የኑሮ ውድነትን ማቃለል፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ውጤታማ የማድረግ፣ ከሰላምና ጸጥታ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ከሕዝብ ጋር በመሆን በሂደት እየተቃለሉ እንዲሄዱ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ማድረጉን ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ ቀሪ ሥራዎችንም በቀጣይ ከሕዝቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን መንግሥት ለመፍታት ርብርቡን እንደሚያስቀጥል በግምገማቸው ወቅት መገለጹን ገልጸዋል።
የኮይሻ ግድብ የለውጡ መንግስት እንደ ሕዳሴ ግድብ የታደገው ፕሮጀክት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Oct 24, 2025 68
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):- የኮይሻ ግድብ የለውጡ መንግስት እንደ ሕዳሴ ግድብ ከታደጋቸው ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማን አስመልክቶ በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት በሰጡት አስተያየት ከዓመታት በፊት የኮይሻ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ መሰረት ከመጣል ባለፈ አፈጻጸሙ በሚፈለገው ደረጃ ላይ እንዳልነበር ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ያለበት የግንባታ ደረጃ ከዚህ ቀደም ከነበረው ከፍተኛ ለውጥ እንዳለው አመልክተዋል። የኮይሻ ግድብ ከኤሌክትሪክ ማመንጨት ባሻገር ለቱሪዝም መስህብነት የሚሆኑ ስራዎች እንደተካተቱ ጠቁመው፤ ሎጆችን ጨምሮ የተለያዩ ግንባታዎችን ማከናወን የሚያስችሉ ተራራዎች እንዳሉ አንስተዋል። የግንባታው ስራ በፍጥነት እየሄደ መሆኑን ጠቅሰው፤ ግድቡ 1ሺህ 800 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።   ኮይሻ ለየት ያሉ በርካታ ተራሮች የሚገኙበትና ትልቁ የኦሞ ወንዝ የሚፈስበት መሆኑን ገልጸው፤ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋ ከተጠቀመች የሚፈለገውን ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል የሚያሳይ እንደሆነም ነው የገለጹት። ኮይሻ ግድብ የለውጡ መንግስት እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከታደጋቸው ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑንም ነው የተናገሩት። ኮይሻ፣ ሃላላ ኬላ እና ጨበራ ጩርጩራ ፓርክ ከኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቱ ጋር ተዳምረው ቱሪዝሙን ማሳደግ የሚችሉ ጸጋዎች መሆናቸውንም አመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለኮይሻ ግድብ ግንባታ መፋጠን ለሰጡት በሳል አመራርም አመስግነዋል።
ኢትዮጵያ ትበለጽጋለች የሚገባትንም ስፍራ ትይዛለች -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 24, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞዋን በማሳካት የሚገባትንም ስፍራ ትይዛለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማን አስመልክቶ በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በለውጡ ዓመታት ትኩረት ከተሰጣቸው ስራዎች መካከል አንዱ ኢትዮጵያንና ጸጋዎቿን በሚገባ ማወቅ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ብቃት እና አቅም በቅጡ መገንዘብ ሀገርን ለመስራት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ጠቅሰው፤ በዚህ ሂደት ውስጥ በርካታ አቅምን የሚገልጡ ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል።   የጨበራ ጩርጩራ ፓርክ እና ኮይሻ የሀገርን አቅም የገለጡና ውጤት የተገኘባቸው ስራዎች መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። ሀገሩን የሚያውቅ እና በሀገሩ ክብር የሚሰማው ሰው ተግቶ ለመስራት እና እያንዳንዷን ቀን ለመለወጥ እድል አድርጎ እንዲወስድ እድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ያየነቻው ፈተናዎችና መከራዎች አጠንክረውን በበለጠ ጽናት ተግተን እንድንስራ እና ውጤት እንድናገኝ አድርገውናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ኢትዮጵያ እንደምትበለጽግና የሚገባትን ስፍራ እንደምትይዝ ምንም ጥርጥር የለውም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህን ራዕይ ለማሳካት የእያንዳንዱን ዜጋ ጥረት እና ድካም እንደሚጠይቅ አመልክተዋል። ተግተን ከሰራን በልጆቻችን ላይ ፍሬውን ለማየት ጊዜው ሩቅ አይደለም ሲሉም ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሶስት ወራት በሁሉም መስኮች ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰው፤ በአንዳንድ መስኮች የተገኘው ውጤት ከተጠበቀው በላይ መሆኑንም አመልክተዋል። የተገኙ ውጤቶች በቀጣይ የሩብ ዓመታት በማስቀጠል ውጤቶችን ማላቅ ከተቻለ የኢትዮጵያን የኃይል ሽግሽግ የሚቀይሩ መሰረታዊ ጉዳዮች የሚከናወኑበት ዓመት እንደሚሆንም ተናግረዋል። የተገኙ ውጤቶችን ለማጽናት በበለጠ ትጋት እና አቅም መስራት እንደሚገባም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አሳስበዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መገናኛ ብዙኃን ልዩነት ሊኖራቸው አይገባም 
Oct 24, 2025 132
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር እና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መገናኛ ብዙኃን ልዩነት ሊኖራቸው እንደማይገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ የሚያስችል አቅም ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞችን ለመፍጠር የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ሥራ አስጀምሯል፡፡ የሚዲያ ልህቀት ማዕከሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት፣ የወል ትርክትና ብልጽግና ላይ የጋራ አቋም ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞችን ማፍራት ያለመ ነው፡፡ በምርጫ ጋዜጠኝነት፣ ውሃ፣ የአቬሽን፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በሰላም ጋዜጠኝነት እና በሌሎች ሀገራዊ ዘርፎች ላይ ጥናትና ምርምር፣ ስልጠናና የማማከር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያውን በምርጫ ጋዜጠኝነት ላይ የሚያተኩር ስልጠና ትናንት አስጀምሯል፡፡   የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ እንዳሉት፤ ብሔራዊ ጥቅም የሀገርን ደህንነት፣ ዋስትና እና ቀጣይነት የሚመለከት አንኳር ጉዳይ ነው፡፡ ሀገራዊ ህልውናና ደህንነት፣ ዕድገትና ብልጽግና፣ ታሪኳንና አስተዋጽኦዋን የሚመጥን ተሰሚነትና ተጽዕኖ ፈጣሪነት፣ የባህልና የፖሊሲ ነጻነት እና ማህበረሰባዊ ልማትና ተጠቃሚነት በሚሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ልዩነት ሊኖር አይገባም ብለዋል፡፡ ብሔራዊ መግባባት የአንድ ሀገር ሰዎችን የሚመለከት መሆኑን በማንሳት፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም መያዝ ለኢትዮጵያውን አዲስ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ዓድዋ ላይ ለነጻነታቸው የከፈሉትን ዋጋ እና ለታላቁ በኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ በአብነት አንስተዋል፡፡   በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ልዩነት ሊኖር እንደማይገባ ገልጸው፤ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች በብሔራዊ ጥቅም ላይ አንድ ዓይነት አቋም በመያዝ ለህብረተሰቡ ግልጽና ገንቢ መረጃ ማቅረብ አለባቸው ብለዋል፡፡ ማዕከሉ የጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት ብሔራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ትልቅ ሚና መወጣቱን ገልጸው፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰጠው ስልጠና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የጎላ አበርክቶ እንዳለው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ጋዜጠኞች በብሔራዊ ጥቅም ላይ የጋራ አቋም እንዲኖራቸው የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡   በሀገር ህልውናና ልማት ላይ በኢትዮጵያውያን መካከል ልዩነት መኖር እንደሌለበት ገልጸው፤ ስልጠናው በኢትዮጵያ ያሉ የሁሉንም መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች ያሳተፈ ነው ብለዋል፡፡ የልህቀት ማዕከሉ ስልጠናውን በምርጫ ጋዜጠኝነት መጀመሩን አንስተው፤ ለሰልጣኞች ቀጣይ ስራቸው ጠቃሚ የምስክር ወረቀት እንዳለው ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያና አሜሪካ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ብሩክ ሀይሉ በሻህ፤ ጋዜጠኝነት መንግስትና ብሔራዊ ጥቅምን የለየ መሆን ይኖርበታል ብለዋል፡፡   በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ የሚደራደር ጋዜጠኛ መኖር የለበትም ያሉት ፕሮፌሰር ብሩክ፤ ኢትዮጵያ በመርህ ላይ ተመስርተው የሚሞግቱ ደፋር ጋዜጠኞች እንደሚያስፈልጓት ገልጸዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን በመርህና በሙያዊ ሥነ ምግባር ታንጸው የሚሰሩት ዘገባ ፖሊሲ ማስቀየር እንደሚችል ገልጸው፤ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል የጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አማካሪ እና የልህቀት ማዕከሉ አስተባባሪ ታምራት ደጀኔ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በምትፈልገው ጉዳይ ሁሉ ሀገሩን ማገልገል፤ ለሀገሩ ብሔራዊ ጥቅም መቆም ከሁሉም ይጠበቃል።   ሁሉም ሙያ ለሀገሩ ብሔራዊ ጥቅም መቆም እንዳለበት ገልጸው፤ የልህቀት ማዕከሉ ሰልጣኞችም ለዜጎች ተጠቃሚነት ዘብ መቆም አለባቸው ብለዋል፡፡ ጋዜጠኞች ያገኙትን መረጃ ሁሉ ከማሰራጨታቸው በፊት ለሀገር የሚኖረውን ጥቅም ግምት ውስጥ አስገብተው መዘገብ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
የሚታይ
የኢትዮጵያ ዕድገት አይቀሬ መሆኑን አመላካች አፈጻጸሞች ተመዝግበዋል
Oct 24, 2025 84
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡- በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ አፈጻጸሞች ስኬታማነት የኢትዮጵያን ብልጽግና አይቀሬነት አመላካች መሆናቸውን ሚኒስትሮች ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ ከሚኒስትሮች ጋር በመሆን በኮይሻ ግድብ አካሂደዋል። ከግምገማው ጎን ለጎንም ኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን ጨምሮ ጨበራ ጩርጩራ የዝሆኖች ዳና ሎጂን ጎብኝተዋል።   በዚሁ ወቅት የሥራና ክኅሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በሰጡት አስተያየት፤ መሪነት ያለንን ዐውቀንና ፀጋችንን ለይተን ወደ ሀብትነት መቀየርን ይፈልጋል ብለዋል። ከዚህ አንጻር ጨበራ ጩርጩራን በማልማት ወደ ሀብትነት የመቀየር ሥራ መሠራቱን ጠቅሰው፤ ይህም አካባቢውን በማስተሳሰር እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል ሲሉ ገልጸዋል። ከፍ ሲልም በቱሪዝሙ ዘርፍ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት አመላክተው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመሪነት ጥበብን ተጠቅመው ካለን በመጀመር መርኅ እየሠሩ መሆናቸውን ያሳያል ነው ያሉት።   ከ100 ቀናት አፈጻጸም ጋር በተያያዘ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በሰጡት አስተያየት ደግሞ፤ በሁሉም መስኮች ተስፋ የሚፈነጥቁ አፈጻጸሞች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። የግብርናው ዕድገት ከሌሎች ዘርፎች ዕድገት ጋር ተሳስሮ በመሠራቱ ተስፋችንን መጨበጥ ጀምረናል ብለዋል። የሕዳሴው ግድብ፣ የወልመል መስኖ፣ የማዳበሪ ፋብሪካ እና ሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶች ተስፋችንን መጨበጥ መጀመራችንን ብሎም የኢትዮጵያ ብልጽግና አይቀሬነት አመላካች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል። አፈጻጸሙ እንደሚያስረዳው የተቀመጡ ግቦች በስኬት እየተከናወኑ ነው፤ የግብርናው ዕድገትም በአርሶና አርብቶ አደሩ ኑሮ ሁሉ የሚገለጥ ሆኗል ነው ያሉት። የተመዘገቡት ውጤቶች የተገኙት በፈተና ውስጥ መሆኑ ደግሞ ሀገራችንን ፈተና ሳይበግራት ስኬታማ ጉዞ ማድረግ መቻሏን እንደሚያሳይ አንስተዋል። አዲስ የሥራ ባህል እየተፈጠረ መሆኑን ዐይቻለሁ ያሉት ሚኒስትሩ፤ ሕዝብን በማሳተፍ ጀምሮ የመጨረስ ዐቅም እያደገ መምጣቱንም ታዝቤያለሁ ብለዋል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ስለኮይሻ እና ጨበራ ጩርጩራ በሰጡት ሐሳብ፤ ካለፈው ዓመት አንጻር ሥራው እያደገ መሆኑን ተመልክቻለሁ ነው ያሉት። አዳዲስ መዳረሻዎች ተገንብተው ለኢኮኖሚ ማመንጨት ተደማሪ ዐቅም እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ የነበራትን ፀጋ ለይቶ እና ዐውቆ ወደ ሀብት መቀየር ጊዜ ይፈልግ ነበር፤ አሁን ጊዜው ሆኖ ወደ ሀብት እንዲቀየሩ እየተደረገ ነው ሲሉም አመላክተዋል። አሁን ላይ የቱሪዝም ሀብት እየሰፋ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በግንባታ ላይ የሚገኙት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ የሰው ልጅ ሊጎበኛቸው የሚገባ መዳረሻዎች እንደሚሆኑም ተናግረዋል። ሀገር ያላትን ዐቅምና ፀጋ በመለየት እየተከናወኑ ባሉ አዳዲስ መዳረሻዎች እና በ100 ቀናት አፈጻጸም በሁሉም ዘርፍ ለተገኙ ስኬቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ሚኒስትሮቹ ገልጸዋል።
በማክሮ ኢኮኖሚውና ኢኮኖሚያዊ ዕድገቱ የተገኘው ስኬት የሦስት ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው - አቶ አደም ፋራህ
Oct 24, 2025 83
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡- በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ከ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም እና የኢኮኖሚ ዕድገት አዝማሚያዎች ጋር በተያያዘ የተገኘው ስኬት የሦስት ቁልፍ ጉዳዮች ድምር ውጤት መሆኑን አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ ከሚኒስትሮች ጋር በመሆን በኮይሻ ግድብ አካሂደዋል። ከግምገማው በኋላም አቶ አደም ፋራህ ከ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም እና የኢኮኖሚ ዕድገት አዝማሚያዎች ጋር በተያያዘ አስተያየት ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በጂኦ ፖለቲካ ውጥረት፣ በኢ-ተገማች የታሪፍ ዲፕሎማሲ፣ በአቅርቦት ሰንሰለት መቆራረጥ ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚ ዕድገት መቀዛቀዝ ብሎም የተዳከመ ማክሮ ኢኮኖሚ ዐውድ በሚታይበት ሁኔታ በሀገራችን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስቀጠል ችለናል ብለዋል።   ለዚህ አመርቂ ውጤት ያበቃን የሦስት ዋና ዋና ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው ብዬ አምናለሁ ሲሉም ገልጸዋል። የመጀመሪያው ከለውጡ ወዲህ የዕይታ ለውጥ(ፓራዳይም ሽፍት) ማምጣት መቻላችን ነው ብለዋል አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያያት። ለስኬታችን ሁለተኛው ምክንያት የአመራሩ የማስፈጸም ዐቅም፣ ትጋትና ቁርጠኝነት መሆኑንም ጠቅሰዋል። እንዲሁም ሦስተኛው የሕዝቡ፣ የግሉ ሴክተር፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ እና ትብብር ማደግ መሆኑን አንስተዋል። መንግሥት ሕዝቡ በተደጋጋሚ ሲያነሳቸው የነበሩትን፤ የኑሮ ውድነትን ማቃለል፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ውጤታማ የማድረግ፣ ከሰላምና ጸጥታ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ከሕዝብ ጋር በመሆን በሂደት እየተቃለሉ እንዲሄዱ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ማድረጉን ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ ቀሪ ሥራዎችንም በቀጣይ ከሕዝቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን መንግሥት ለመፍታት ርብርቡን እንደሚያስቀጥል በግምገማቸው ወቅት መገለጹን ገልጸዋል።
የኮይሻ ግድብ የለውጡ መንግስት እንደ ሕዳሴ ግድብ የታደገው ፕሮጀክት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Oct 24, 2025 68
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):- የኮይሻ ግድብ የለውጡ መንግስት እንደ ሕዳሴ ግድብ ከታደጋቸው ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማን አስመልክቶ በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት በሰጡት አስተያየት ከዓመታት በፊት የኮይሻ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ መሰረት ከመጣል ባለፈ አፈጻጸሙ በሚፈለገው ደረጃ ላይ እንዳልነበር ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ያለበት የግንባታ ደረጃ ከዚህ ቀደም ከነበረው ከፍተኛ ለውጥ እንዳለው አመልክተዋል። የኮይሻ ግድብ ከኤሌክትሪክ ማመንጨት ባሻገር ለቱሪዝም መስህብነት የሚሆኑ ስራዎች እንደተካተቱ ጠቁመው፤ ሎጆችን ጨምሮ የተለያዩ ግንባታዎችን ማከናወን የሚያስችሉ ተራራዎች እንዳሉ አንስተዋል። የግንባታው ስራ በፍጥነት እየሄደ መሆኑን ጠቅሰው፤ ግድቡ 1ሺህ 800 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።   ኮይሻ ለየት ያሉ በርካታ ተራሮች የሚገኙበትና ትልቁ የኦሞ ወንዝ የሚፈስበት መሆኑን ገልጸው፤ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋ ከተጠቀመች የሚፈለገውን ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል የሚያሳይ እንደሆነም ነው የገለጹት። ኮይሻ ግድብ የለውጡ መንግስት እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከታደጋቸው ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑንም ነው የተናገሩት። ኮይሻ፣ ሃላላ ኬላ እና ጨበራ ጩርጩራ ፓርክ ከኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቱ ጋር ተዳምረው ቱሪዝሙን ማሳደግ የሚችሉ ጸጋዎች መሆናቸውንም አመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለኮይሻ ግድብ ግንባታ መፋጠን ለሰጡት በሳል አመራርም አመስግነዋል።
ኢትዮጵያ ትበለጽጋለች የሚገባትንም ስፍራ ትይዛለች -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 24, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞዋን በማሳካት የሚገባትንም ስፍራ ትይዛለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማን አስመልክቶ በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በለውጡ ዓመታት ትኩረት ከተሰጣቸው ስራዎች መካከል አንዱ ኢትዮጵያንና ጸጋዎቿን በሚገባ ማወቅ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ብቃት እና አቅም በቅጡ መገንዘብ ሀገርን ለመስራት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ጠቅሰው፤ በዚህ ሂደት ውስጥ በርካታ አቅምን የሚገልጡ ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል።   የጨበራ ጩርጩራ ፓርክ እና ኮይሻ የሀገርን አቅም የገለጡና ውጤት የተገኘባቸው ስራዎች መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። ሀገሩን የሚያውቅ እና በሀገሩ ክብር የሚሰማው ሰው ተግቶ ለመስራት እና እያንዳንዷን ቀን ለመለወጥ እድል አድርጎ እንዲወስድ እድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ያየነቻው ፈተናዎችና መከራዎች አጠንክረውን በበለጠ ጽናት ተግተን እንድንስራ እና ውጤት እንድናገኝ አድርገውናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ኢትዮጵያ እንደምትበለጽግና የሚገባትን ስፍራ እንደምትይዝ ምንም ጥርጥር የለውም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህን ራዕይ ለማሳካት የእያንዳንዱን ዜጋ ጥረት እና ድካም እንደሚጠይቅ አመልክተዋል። ተግተን ከሰራን በልጆቻችን ላይ ፍሬውን ለማየት ጊዜው ሩቅ አይደለም ሲሉም ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሶስት ወራት በሁሉም መስኮች ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰው፤ በአንዳንድ መስኮች የተገኘው ውጤት ከተጠበቀው በላይ መሆኑንም አመልክተዋል። የተገኙ ውጤቶች በቀጣይ የሩብ ዓመታት በማስቀጠል ውጤቶችን ማላቅ ከተቻለ የኢትዮጵያን የኃይል ሽግሽግ የሚቀይሩ መሰረታዊ ጉዳዮች የሚከናወኑበት ዓመት እንደሚሆንም ተናግረዋል። የተገኙ ውጤቶችን ለማጽናት በበለጠ ትጋት እና አቅም መስራት እንደሚገባም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አሳስበዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መገናኛ ብዙኃን ልዩነት ሊኖራቸው አይገባም 
Oct 24, 2025 132
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር እና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መገናኛ ብዙኃን ልዩነት ሊኖራቸው እንደማይገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ የሚያስችል አቅም ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞችን ለመፍጠር የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ሥራ አስጀምሯል፡፡ የሚዲያ ልህቀት ማዕከሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት፣ የወል ትርክትና ብልጽግና ላይ የጋራ አቋም ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞችን ማፍራት ያለመ ነው፡፡ በምርጫ ጋዜጠኝነት፣ ውሃ፣ የአቬሽን፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በሰላም ጋዜጠኝነት እና በሌሎች ሀገራዊ ዘርፎች ላይ ጥናትና ምርምር፣ ስልጠናና የማማከር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያውን በምርጫ ጋዜጠኝነት ላይ የሚያተኩር ስልጠና ትናንት አስጀምሯል፡፡   የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ እንዳሉት፤ ብሔራዊ ጥቅም የሀገርን ደህንነት፣ ዋስትና እና ቀጣይነት የሚመለከት አንኳር ጉዳይ ነው፡፡ ሀገራዊ ህልውናና ደህንነት፣ ዕድገትና ብልጽግና፣ ታሪኳንና አስተዋጽኦዋን የሚመጥን ተሰሚነትና ተጽዕኖ ፈጣሪነት፣ የባህልና የፖሊሲ ነጻነት እና ማህበረሰባዊ ልማትና ተጠቃሚነት በሚሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ልዩነት ሊኖር አይገባም ብለዋል፡፡ ብሔራዊ መግባባት የአንድ ሀገር ሰዎችን የሚመለከት መሆኑን በማንሳት፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም መያዝ ለኢትዮጵያውን አዲስ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ዓድዋ ላይ ለነጻነታቸው የከፈሉትን ዋጋ እና ለታላቁ በኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ በአብነት አንስተዋል፡፡   በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ልዩነት ሊኖር እንደማይገባ ገልጸው፤ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች በብሔራዊ ጥቅም ላይ አንድ ዓይነት አቋም በመያዝ ለህብረተሰቡ ግልጽና ገንቢ መረጃ ማቅረብ አለባቸው ብለዋል፡፡ ማዕከሉ የጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት ብሔራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ትልቅ ሚና መወጣቱን ገልጸው፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰጠው ስልጠና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የጎላ አበርክቶ እንዳለው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ጋዜጠኞች በብሔራዊ ጥቅም ላይ የጋራ አቋም እንዲኖራቸው የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡   በሀገር ህልውናና ልማት ላይ በኢትዮጵያውያን መካከል ልዩነት መኖር እንደሌለበት ገልጸው፤ ስልጠናው በኢትዮጵያ ያሉ የሁሉንም መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች ያሳተፈ ነው ብለዋል፡፡ የልህቀት ማዕከሉ ስልጠናውን በምርጫ ጋዜጠኝነት መጀመሩን አንስተው፤ ለሰልጣኞች ቀጣይ ስራቸው ጠቃሚ የምስክር ወረቀት እንዳለው ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያና አሜሪካ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ብሩክ ሀይሉ በሻህ፤ ጋዜጠኝነት መንግስትና ብሔራዊ ጥቅምን የለየ መሆን ይኖርበታል ብለዋል፡፡   በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ የሚደራደር ጋዜጠኛ መኖር የለበትም ያሉት ፕሮፌሰር ብሩክ፤ ኢትዮጵያ በመርህ ላይ ተመስርተው የሚሞግቱ ደፋር ጋዜጠኞች እንደሚያስፈልጓት ገልጸዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን በመርህና በሙያዊ ሥነ ምግባር ታንጸው የሚሰሩት ዘገባ ፖሊሲ ማስቀየር እንደሚችል ገልጸው፤ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል የጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አማካሪ እና የልህቀት ማዕከሉ አስተባባሪ ታምራት ደጀኔ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በምትፈልገው ጉዳይ ሁሉ ሀገሩን ማገልገል፤ ለሀገሩ ብሔራዊ ጥቅም መቆም ከሁሉም ይጠበቃል።   ሁሉም ሙያ ለሀገሩ ብሔራዊ ጥቅም መቆም እንዳለበት ገልጸው፤ የልህቀት ማዕከሉ ሰልጣኞችም ለዜጎች ተጠቃሚነት ዘብ መቆም አለባቸው ብለዋል፡፡ ጋዜጠኞች ያገኙትን መረጃ ሁሉ ከማሰራጨታቸው በፊት ለሀገር የሚኖረውን ጥቅም ግምት ውስጥ አስገብተው መዘገብ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በማክሮ ኢኮኖሚውና ኢኮኖሚያዊ ዕድገቱ የተገኘው ስኬት የሦስት ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው - አቶ አደም ፋራህ
Oct 24, 2025 83
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡- በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ከ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም እና የኢኮኖሚ ዕድገት አዝማሚያዎች ጋር በተያያዘ የተገኘው ስኬት የሦስት ቁልፍ ጉዳዮች ድምር ውጤት መሆኑን አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ ከሚኒስትሮች ጋር በመሆን በኮይሻ ግድብ አካሂደዋል። ከግምገማው በኋላም አቶ አደም ፋራህ ከ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም እና የኢኮኖሚ ዕድገት አዝማሚያዎች ጋር በተያያዘ አስተያየት ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በጂኦ ፖለቲካ ውጥረት፣ በኢ-ተገማች የታሪፍ ዲፕሎማሲ፣ በአቅርቦት ሰንሰለት መቆራረጥ ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚ ዕድገት መቀዛቀዝ ብሎም የተዳከመ ማክሮ ኢኮኖሚ ዐውድ በሚታይበት ሁኔታ በሀገራችን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስቀጠል ችለናል ብለዋል።   ለዚህ አመርቂ ውጤት ያበቃን የሦስት ዋና ዋና ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው ብዬ አምናለሁ ሲሉም ገልጸዋል። የመጀመሪያው ከለውጡ ወዲህ የዕይታ ለውጥ(ፓራዳይም ሽፍት) ማምጣት መቻላችን ነው ብለዋል አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያያት። ለስኬታችን ሁለተኛው ምክንያት የአመራሩ የማስፈጸም ዐቅም፣ ትጋትና ቁርጠኝነት መሆኑንም ጠቅሰዋል። እንዲሁም ሦስተኛው የሕዝቡ፣ የግሉ ሴክተር፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ እና ትብብር ማደግ መሆኑን አንስተዋል። መንግሥት ሕዝቡ በተደጋጋሚ ሲያነሳቸው የነበሩትን፤ የኑሮ ውድነትን ማቃለል፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ውጤታማ የማድረግ፣ ከሰላምና ጸጥታ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ከሕዝብ ጋር በመሆን በሂደት እየተቃለሉ እንዲሄዱ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ማድረጉን ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ ቀሪ ሥራዎችንም በቀጣይ ከሕዝቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን መንግሥት ለመፍታት ርብርቡን እንደሚያስቀጥል በግምገማቸው ወቅት መገለጹን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መገናኛ ብዙኃን ልዩነት ሊኖራቸው አይገባም 
Oct 24, 2025 132
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር እና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መገናኛ ብዙኃን ልዩነት ሊኖራቸው እንደማይገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ የሚያስችል አቅም ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞችን ለመፍጠር የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ሥራ አስጀምሯል፡፡ የሚዲያ ልህቀት ማዕከሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት፣ የወል ትርክትና ብልጽግና ላይ የጋራ አቋም ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞችን ማፍራት ያለመ ነው፡፡ በምርጫ ጋዜጠኝነት፣ ውሃ፣ የአቬሽን፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በሰላም ጋዜጠኝነት እና በሌሎች ሀገራዊ ዘርፎች ላይ ጥናትና ምርምር፣ ስልጠናና የማማከር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያውን በምርጫ ጋዜጠኝነት ላይ የሚያተኩር ስልጠና ትናንት አስጀምሯል፡፡   የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ እንዳሉት፤ ብሔራዊ ጥቅም የሀገርን ደህንነት፣ ዋስትና እና ቀጣይነት የሚመለከት አንኳር ጉዳይ ነው፡፡ ሀገራዊ ህልውናና ደህንነት፣ ዕድገትና ብልጽግና፣ ታሪኳንና አስተዋጽኦዋን የሚመጥን ተሰሚነትና ተጽዕኖ ፈጣሪነት፣ የባህልና የፖሊሲ ነጻነት እና ማህበረሰባዊ ልማትና ተጠቃሚነት በሚሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ልዩነት ሊኖር አይገባም ብለዋል፡፡ ብሔራዊ መግባባት የአንድ ሀገር ሰዎችን የሚመለከት መሆኑን በማንሳት፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም መያዝ ለኢትዮጵያውን አዲስ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ዓድዋ ላይ ለነጻነታቸው የከፈሉትን ዋጋ እና ለታላቁ በኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ በአብነት አንስተዋል፡፡   በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ልዩነት ሊኖር እንደማይገባ ገልጸው፤ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች በብሔራዊ ጥቅም ላይ አንድ ዓይነት አቋም በመያዝ ለህብረተሰቡ ግልጽና ገንቢ መረጃ ማቅረብ አለባቸው ብለዋል፡፡ ማዕከሉ የጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት ብሔራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ትልቅ ሚና መወጣቱን ገልጸው፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰጠው ስልጠና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የጎላ አበርክቶ እንዳለው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ጋዜጠኞች በብሔራዊ ጥቅም ላይ የጋራ አቋም እንዲኖራቸው የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡   በሀገር ህልውናና ልማት ላይ በኢትዮጵያውያን መካከል ልዩነት መኖር እንደሌለበት ገልጸው፤ ስልጠናው በኢትዮጵያ ያሉ የሁሉንም መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች ያሳተፈ ነው ብለዋል፡፡ የልህቀት ማዕከሉ ስልጠናውን በምርጫ ጋዜጠኝነት መጀመሩን አንስተው፤ ለሰልጣኞች ቀጣይ ስራቸው ጠቃሚ የምስክር ወረቀት እንዳለው ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያና አሜሪካ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ብሩክ ሀይሉ በሻህ፤ ጋዜጠኝነት መንግስትና ብሔራዊ ጥቅምን የለየ መሆን ይኖርበታል ብለዋል፡፡   በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ የሚደራደር ጋዜጠኛ መኖር የለበትም ያሉት ፕሮፌሰር ብሩክ፤ ኢትዮጵያ በመርህ ላይ ተመስርተው የሚሞግቱ ደፋር ጋዜጠኞች እንደሚያስፈልጓት ገልጸዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን በመርህና በሙያዊ ሥነ ምግባር ታንጸው የሚሰሩት ዘገባ ፖሊሲ ማስቀየር እንደሚችል ገልጸው፤ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል የጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አማካሪ እና የልህቀት ማዕከሉ አስተባባሪ ታምራት ደጀኔ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በምትፈልገው ጉዳይ ሁሉ ሀገሩን ማገልገል፤ ለሀገሩ ብሔራዊ ጥቅም መቆም ከሁሉም ይጠበቃል።   ሁሉም ሙያ ለሀገሩ ብሔራዊ ጥቅም መቆም እንዳለበት ገልጸው፤ የልህቀት ማዕከሉ ሰልጣኞችም ለዜጎች ተጠቃሚነት ዘብ መቆም አለባቸው ብለዋል፡፡ ጋዜጠኞች ያገኙትን መረጃ ሁሉ ከማሰራጨታቸው በፊት ለሀገር የሚኖረውን ጥቅም ግምት ውስጥ አስገብተው መዘገብ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የባህር በርን ጨምሮ ቀሪ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ስብራቶችን ለመጠገን ከባለድርሻ አካላት ጋር በትጋት እንደሚሰራ ገለጸ
Oct 24, 2025 100
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):- የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የባህር በርን ጨምሮ ቀሪ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ስብራቶችን ለመጠገን ከባለድርሻ አካላት ጋር በትጋት እንደሚሰራ ገለጸ። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮችና የፓርቲ አጀንዳዎች ላይ መክሮ አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጸዋል። ፓርቲው የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና የማረጋገጥ ራዕይን ሰንቆ ወደ ተግባር መግባቱን አውስተው፤ ባለፉት ዓመታት ለህዝብ ቃል የገባውን በውጤታማነት እየፈጸመ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን ቀሪ ስብራቶች ለመጠገን ከባለድርሻ አካላት ጋር በትጋት እንደሚሰራ ተናግረው፤ ብሔራዊ ጥቅምን ማዕከል ያደረጉ የተሟላ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንደሚወጣ ገልፀዋል። በኢኮኖሚው ዘርፍ ባለፉት ዓመታት በተሠሩ የልማት ስራዎች ከፍተኛ ውጤት መምጣቱን ገልጸው፤ ለአብነትም ባለፈው ዓመት የ9 ነጥብ 2 በመቶ እድገት መመዝገቡን ተናግረዋል። የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር እየተረጋገጠ መሆኑን ሥራ አስፈጻሚው መገምገሙን ጠቅሰው፤ በዚህም ኢኮኖሚው ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪና ዘመናዊ አገልግሎት እየተሸጋገረ ይገኛል ብለዋል። በገቢ ማሰባሰብ፣ በወጭ ንግድ እና በተኪ ምርት አመርቂ ውጤት መመዝገቡን በማንሳት አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱ ፈጣን ብቻ ሳይሆን አካታች፣ ጥራት ያለውና የህዝቡን ኑሮ በተጨባጭ እያሻሻለ መሆኑን ጠቅሰዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን በተጀመሩ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸው፤ በሰው ተኮር ስራዎችም በርካታ አቅመ ደካማ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። በቀጣይም ተረጂነትን የማስወገድ፣ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለማሟላት በቂ ፈንድ የመያዝ እንዲሁም ብሄራዊ የመጠባበቂያ ክምችትን በራስ አቅም የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የሰላም እና የፖለቲካ ጉዳዮችን መገምገሙን በማንሳት ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የበኩሉን ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆኑን ማረጋገጡን ጠቅሰዋል። መጪው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተአማኒ፣ ግልጽና አሳታፊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ ፓርቲው የድርሻውን እንደሚወጣም ገልጸዋል። ውስን የሰላምና ፀጥታ ችግር የነበረባቸውን አካባቢዎችን ለማረጋጋት መንግስትና ህዝብ በጋራ በሰሩት ስራ ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። ማንኛውም የፖለቲካ ጥያቄ ያለው አካል ጥያቄውን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ምህዳር መፈጠሩን ገልጸው፤ ፓርቲውና የሚመራው መንግስት ሁልጊዜም በራቸው ለሰላም ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል። በስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ስብሰባው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ የተቀመጠው አቅጣጫ ወደ ተጨባጭ ተግባር መገባቱን ተገምግሟል ብለዋል። በዚህም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማስፋትና የዲጂታላይዜሽን ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን አመልክተው፤ እስካሁንም 16 ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት እየሠጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በመሶብ ማዕከላት የህዝቡ እርካታ ወደ 95 መቶ መድረሱን ገልጸው፤ የመሶብ ማዕከላትን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓም ወደ መቶ ለማድረስ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አቅጣጫ ማስቀመጡን ተናግረዋል። ብልፅግና ፓርቲ ጠንካራ መንግስትና ሀገር ለመገንባት የያዘውን ግብ ለማሳካት የአመራርና አባላቱን አቅም የሚያጎለብቱ የተለያዩ ተግባራትን ማከናወኑንም ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ አመራርና አባላቱ በተሠጣቸው ተልዕኮ ልክ በየደረጃው የመገምገም ስራ ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፤ በምዘናው መሠረት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡት እውቅና መሰጠቱን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የተሰጣቸውን ሀገራዊና የፓርቲ ተልዕኮ በአግባቡ ባልተወጡ አመራሮች ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን መወሰዱን ተናግረው፤ ፓርቲው ህዝብና ሀገርን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራችውን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው 11ኛው የጣና ፎረም በስኬት መጠናቀቅ የክልሉ ከተሞች አህጉራዊና ዓለም አቀፍዊ መድረኮችን በብቃት የማስተናገድ አቅም ያሳየ ነው
Oct 24, 2025 113
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦ በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው 11ኛው የጣና ፎረም በስኬት መጠናቀቅ የክልሉ ከተሞች አህጉራዊና ዓለም አቀፍዊ መድረኮችን በብቃት የማስተናገድ አቅም ያሳየ መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ(ዶ/ር) ገለጹ። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው መድረክ ተጠናቋል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እንዲሁም የአፍሪካ ሀገራት፣ የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተማ በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ(ዶ/ር)፤ በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው 11ኛውን የጣና ፎረም ጉባኤ አስክመልክቶ ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥተዋል። የፎረሙ አስተባባሪ ኮሚቴ በአዲስ አበባና ባሕር ዳር ከተማ ለማካሄድ ውሳኔ ካሳለፈበት ጊዜ ጀምሮ በክልል ደረጃ ኮሚቴ በማደራጀት ውጤታማ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኅይል ኮሚቴም ከፎረሙ ዋዜማ ጀምሮ በዕቅድ የተመራ ዝግጅት በማድረግ የተሳካ ስራ መስራቱንም ተናግረዋል። በዚህም በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው ፎረም በተደረገው ዝግጅት ልክ በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል። የጣና ፎረም የባሕር ዳር ከተማ ተሳታፊ እንግዶችን ከአቀባበል ጀምሮ አጠቃላይ ሂደት ደስተኞች እንዲሆኑ ለማድረግ በትጋት ሲሰራ መቆየቱን አመልክተዋል። 11ኛው የጣና ፎረም ስኬት ኃላፊነታቸውን ለተወጡ የፌዴራልና የክልሉ የጸጥታና ደህንነት ግብረ ኃይል፣ እንግዳ ተቀባዩ የባህር ዳር ከተማ ህዝብ እና ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። በባሕርዳር ከተማ በስኬት የተካሄደው አህጉራዊ ፎረም የክልሉ ከተሞች አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ መድረኮችን በብቃት ማስተናገድ እንደሚችሉ ትምህርት የሰጠ መሆኑንም ገልጸዋል።
11ኛው የጣና ፎረም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ያላትን የላቀ አስተዋጽኦ የምታጸናበት ነው-አምባሳደር ነብያት ጌታቸው
Oct 24, 2025 156
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-11ኛው የጣና ፎረም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ያላትን የላቀ አስተዋጽኦ የምታጸናበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለጹ። ከጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣ የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተማ በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የጣና ፎረም በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ጉዳዮች ላይ በመምከር መፍትሔ አመላካች ምክረ ሃሳቦች የሚቀርቡበት አህጉራዊ መድረክ ነው ብለዋል። በፎረሙ ላይ የመንግስት አካላት፣ሚኒስትሮች፣አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ምሁራንና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት መሆኑን ተናግረዋል። "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ መካሄድ የጀመረው የዘንድሮው የጣና ፎረም አፍሪካ በተለዋዋጭ የዓለም ሁኔታ የሚኖራትን ሚና እንደሚዳስስ አንስተዋል። ወቅታዊው የዓለም ሁኔታ የፖለቲካ ፉክክር እየከረረና የባለብዙ ወገን ዓለም አቀፍ ትብብር እየላሉ የመጡበት መሆኑን አስረድተዋል። በጣና ፎረም አፍሪካ ውጥረት በተሞላበት ዓለም አቀፍ ሁኔታ የሰላምና ደኅንነት እንዲሁም ሌሎች አጀንዳዎች ላይ ያሏትን መፍትሔዎች እንደምታራምድ አብራርተዋል። የጣና ፎረም ትኩረት አፍሪካዊ መፍትሔዎች ላይ ነው ያሉት አምባሳደር ነቢያት፥ በዚህም ከአፍሪካውያን የመነጩ የሰላምና ደኅንነት የመፍትሔ ሃሳቦች የሚንሸራሸሩበት መድረክ ነው ብለዋል። በመድረኩም ለአፍሪካውያን የፖሊሲ አውጪዎች ምክረ ሃሳብ የሚሆኑ ሀሳቦች የሚወጡበት መሆኑንም ገልጸዋል። ለ11ኛ ጊዜ በባሕር ዳርና በአዲስ አበባ የሚካሄደው የጣና ፎረም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ያላትን የላቀ አስተዋጽኦ የምታጸናበት መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው።
በዞኑ የልማት ስራዎችን ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የተጠናከረ እርምጃ ይቀጥላል
Oct 24, 2025 99
ደሴ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡-በደቡብ ወሎ ዞን የልማት ስራዎችን ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት በሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የተጠናከረ እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ። የደቡብ ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አሊ ይማም፥በዞኑ ያለውን ወቅታዊ የሰላም ሁኔታ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በዞኑ የሰላምና ልማት ጉዳይ የሁሉም አጀንዳ ሆኖ እየተሰራበት መሆኑን አንስተዋል። አሁን ላይ አስተማማኝ ሰላም መኖሩንና የልማት ስራዎችም ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል። የፅንፈኛ ቡድኑ የጥፋት ተላላኪዎች በተለያዩ አጋጣሚዎች በስውር በመንቀሳቀስ ዘረፋና እገታ ለመፈፀም ሞክረው በሕዝቡ ትብብርና በጸጥታ ኃይሉ ጥብቅ ክትትል እርምጃ የተወሰደባቸው መሆኑን አስታውሰዋል። በመሆኑም አሁን ላይ በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በመፈጠሩ የልማት ስራዎችም ተጠናክረው መቀጠላቸውን አረጋግጠዋል። የፅንፈኛው ቡድን ዓላማው መዝረፍና ሰዎችን ማገት መሆኑን ሕዝቡ በአግባቡ በመረዳቱ የሰላሙ ጠባቂ ሆኖ መቆሙን ተናግረዋል። በዞኑ የልማት ስራዎችን ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት በሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የተጠናከረ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በአዲሱ የዓለም ሥርዓት የአፍሪካን እጣ ፋንታ የሚወስን የተሻለ አቅጣጫ መተለም ይኖርብናል-አቶ አረጋ ከበደ
Oct 24, 2025 142
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦በአዲሱ የዓለም ሥርዓት የአፍሪካን እጣ ፋንታ የሚወስን የተሻለ አቅጣጫ መተለም ይኖርብናል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል።   በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣ የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተማ በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፎረሙን በከፈቱበት ወቅት፥ ፎረሙ ለዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች አህጉራዊ ምክረ ሀሳቦችን በመፍትሄነት ማመላከት የሚያስችል ነው። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስተማማኝ፣የበለጸገና የተረጋጋ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምኅዳር ለመፍጠር ጥረት ማድረግ እንደሚኖርበት ገልጸዋል። በአዲሱ የዓለም ሥርዓት የአፍሪካን እጣ ፋንታ የሚወስን የተሻለ አቅጣጫ መተለም ይኖርብናል ብለዋል።   የጣና ፎረም መድረክ የአፍሪካን የተፈጥሮ ሀብቶች ለአፍሪካዊያን የኢንዱስትሪ፣ የግብርና ትራንስፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ለመጠቀም በሚቻልባቸው መንገዶች የራሱን ድርሻ እንደሚወጣ ገልጸዋል። የአፍሪካ ወጣቶችን ፈጣንና ተለዋዋጭ የዓለም ጂኦፖለቲካ የቴክኖሎጂ ጥበባዊ የተጠቃሚነት አሰላለፍ ለመፍጠር መልካም አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል። የጣና ፎረም በባሕር ዳር እንዲካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩ የፌደራልና የክልል እንዲሁም አህጉራዊ ተባባሪ ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው። በፎረሙ ላይ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች ምክክር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በጉጂ ዞን የሰፈነው ሰላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ አግዟል-የጉጂ አባ ገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች
Oct 24, 2025 136
አዶላ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦በጉጂ ዞን የሰፈነው ሰላም የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ ማስቻሉን የጉጂ አባ ገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ፡፡ በዞኑ የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ ታጣቂዎች የተሀድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸው ተመልክቷል፡፡ የጉጂ ሆኩ አባገዳ ገናሌ አጋ በአካባቢው ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን አልምቶ ለመጠቀምና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ አለመግባባቶችን በውይይት መፍታት ይገባል ብለዋል። በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የተሳሳተ መንገድ የተከተሉ ወገኖች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመጡ መንግስት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ በዚህም በአካባቢያቸው በርካታ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪውን በመቀበል ሰርቶ ለመለወጥ ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውን ነው የገለጹት፡፡ ይህም የአካባቢውን ሰላም በማጠናከር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የጉጂ አባገዳ አባል ኡዴሳ አጋ በበኩላቸው፥ ቂምና በቀልን ትተን በመቻቻልና በመረዳዳት ለሀገር ሰላምና ልማት በጋራ ቆመን ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ ለዚህም በአካባቢያቸው ለህብረተሰቡ የሰላምን ዋጋ በማስተማርና የታጠቁ አካላትም የሰላምን መንገድ በመምረጥ ወገኖቻቸውን በልማት እንዲክሱ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። በመንግስት የጸጥታ አካላትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ ሰላምና መረጋጋት እየተጠናከረ መምጣቱ የአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እየተሳለጠ መምጣቱን አንስተዋል፡፡ የመንግስትን የሰላም ጥሪና የአባቶችን ምክር ተቀብለው ወደህብረተሰቡ የተቀላቀሉ ታጣቂዎችም ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ ሌላው አባገዳና የሀገር ሽማግሌ አኖሌ ኖቶ በአካባቢው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንና ልማት እንዲፋጠን የበኩላቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአካባቢውን ማህበረሰብ በሰላም አስፈላጊነትና ችግሮችን በውይይት መፍታት ላይ ከማስተማር ጀምሮ ለዘላቂ ሰላም ከመንግስት ጋር በመቀራረብ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግርዋል። የዞኑ አስተዳደርና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ቦጌ ታፈሰ በበኩላቸው፥ መንግስት አለመግባባቶች በውይይት እንዲፈቱ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ሲያደርግ እንደነበረና ዛሬም ማስቀጠሉን አስታውሰዋል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን አባገዳዎች፣የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የዞኑን ህዝብ ያሳተፈ የሰላም ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም የመንግስትን የሰላም አማራጭ የተቀበሉ ከ200 በላይ ታጣቂዎችና ዘጠኝ አመራሮቻቸው የታሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውን ገልጸዋል። በቅርቡም የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ ሌሎች ታጣቂዎች የበደሉትን ህዝብ ለመካስ የተሀድሶ ስልጠና በመውሰድ ላይ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት በዞኑ ሰላምና መረጋጋት በመፈጠሩ ሁለንተናዊ የልማትና የማህበራዊ እንቅስቃሴ በመፋጠን ላይ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ፖለቲካ
በማክሮ ኢኮኖሚውና ኢኮኖሚያዊ ዕድገቱ የተገኘው ስኬት የሦስት ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው - አቶ አደም ፋራህ
Oct 24, 2025 83
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡- በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ከ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም እና የኢኮኖሚ ዕድገት አዝማሚያዎች ጋር በተያያዘ የተገኘው ስኬት የሦስት ቁልፍ ጉዳዮች ድምር ውጤት መሆኑን አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ ከሚኒስትሮች ጋር በመሆን በኮይሻ ግድብ አካሂደዋል። ከግምገማው በኋላም አቶ አደም ፋራህ ከ100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም እና የኢኮኖሚ ዕድገት አዝማሚያዎች ጋር በተያያዘ አስተያየት ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በጂኦ ፖለቲካ ውጥረት፣ በኢ-ተገማች የታሪፍ ዲፕሎማሲ፣ በአቅርቦት ሰንሰለት መቆራረጥ ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚ ዕድገት መቀዛቀዝ ብሎም የተዳከመ ማክሮ ኢኮኖሚ ዐውድ በሚታይበት ሁኔታ በሀገራችን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስቀጠል ችለናል ብለዋል።   ለዚህ አመርቂ ውጤት ያበቃን የሦስት ዋና ዋና ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው ብዬ አምናለሁ ሲሉም ገልጸዋል። የመጀመሪያው ከለውጡ ወዲህ የዕይታ ለውጥ(ፓራዳይም ሽፍት) ማምጣት መቻላችን ነው ብለዋል አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያያት። ለስኬታችን ሁለተኛው ምክንያት የአመራሩ የማስፈጸም ዐቅም፣ ትጋትና ቁርጠኝነት መሆኑንም ጠቅሰዋል። እንዲሁም ሦስተኛው የሕዝቡ፣ የግሉ ሴክተር፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ እና ትብብር ማደግ መሆኑን አንስተዋል። መንግሥት ሕዝቡ በተደጋጋሚ ሲያነሳቸው የነበሩትን፤ የኑሮ ውድነትን ማቃለል፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ውጤታማ የማድረግ፣ ከሰላምና ጸጥታ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ከሕዝብ ጋር በመሆን በሂደት እየተቃለሉ እንዲሄዱ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ማድረጉን ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ ቀሪ ሥራዎችንም በቀጣይ ከሕዝቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን መንግሥት ለመፍታት ርብርቡን እንደሚያስቀጥል በግምገማቸው ወቅት መገለጹን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መገናኛ ብዙኃን ልዩነት ሊኖራቸው አይገባም 
Oct 24, 2025 132
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር እና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር መገናኛ ብዙኃን ልዩነት ሊኖራቸው እንደማይገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ የሚያስችል አቅም ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞችን ለመፍጠር የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ሥራ አስጀምሯል፡፡ የሚዲያ ልህቀት ማዕከሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት፣ የወል ትርክትና ብልጽግና ላይ የጋራ አቋም ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞችን ማፍራት ያለመ ነው፡፡ በምርጫ ጋዜጠኝነት፣ ውሃ፣ የአቬሽን፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በሰላም ጋዜጠኝነት እና በሌሎች ሀገራዊ ዘርፎች ላይ ጥናትና ምርምር፣ ስልጠናና የማማከር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያውን በምርጫ ጋዜጠኝነት ላይ የሚያተኩር ስልጠና ትናንት አስጀምሯል፡፡   የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ እንዳሉት፤ ብሔራዊ ጥቅም የሀገርን ደህንነት፣ ዋስትና እና ቀጣይነት የሚመለከት አንኳር ጉዳይ ነው፡፡ ሀገራዊ ህልውናና ደህንነት፣ ዕድገትና ብልጽግና፣ ታሪኳንና አስተዋጽኦዋን የሚመጥን ተሰሚነትና ተጽዕኖ ፈጣሪነት፣ የባህልና የፖሊሲ ነጻነት እና ማህበረሰባዊ ልማትና ተጠቃሚነት በሚሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ልዩነት ሊኖር አይገባም ብለዋል፡፡ ብሔራዊ መግባባት የአንድ ሀገር ሰዎችን የሚመለከት መሆኑን በማንሳት፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም መያዝ ለኢትዮጵያውን አዲስ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ዓድዋ ላይ ለነጻነታቸው የከፈሉትን ዋጋ እና ለታላቁ በኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ በአብነት አንስተዋል፡፡   በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ልዩነት ሊኖር እንደማይገባ ገልጸው፤ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች በብሔራዊ ጥቅም ላይ አንድ ዓይነት አቋም በመያዝ ለህብረተሰቡ ግልጽና ገንቢ መረጃ ማቅረብ አለባቸው ብለዋል፡፡ ማዕከሉ የጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት ብሔራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ትልቅ ሚና መወጣቱን ገልጸው፤ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰጠው ስልጠና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የጎላ አበርክቶ እንዳለው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ጋዜጠኞች በብሔራዊ ጥቅም ላይ የጋራ አቋም እንዲኖራቸው የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡   በሀገር ህልውናና ልማት ላይ በኢትዮጵያውያን መካከል ልዩነት መኖር እንደሌለበት ገልጸው፤ ስልጠናው በኢትዮጵያ ያሉ የሁሉንም መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች ያሳተፈ ነው ብለዋል፡፡ የልህቀት ማዕከሉ ስልጠናውን በምርጫ ጋዜጠኝነት መጀመሩን አንስተው፤ ለሰልጣኞች ቀጣይ ስራቸው ጠቃሚ የምስክር ወረቀት እንዳለው ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያና አሜሪካ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ብሩክ ሀይሉ በሻህ፤ ጋዜጠኝነት መንግስትና ብሔራዊ ጥቅምን የለየ መሆን ይኖርበታል ብለዋል፡፡   በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ የሚደራደር ጋዜጠኛ መኖር የለበትም ያሉት ፕሮፌሰር ብሩክ፤ ኢትዮጵያ በመርህ ላይ ተመስርተው የሚሞግቱ ደፋር ጋዜጠኞች እንደሚያስፈልጓት ገልጸዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን በመርህና በሙያዊ ሥነ ምግባር ታንጸው የሚሰሩት ዘገባ ፖሊሲ ማስቀየር እንደሚችል ገልጸው፤ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል የጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አማካሪ እና የልህቀት ማዕከሉ አስተባባሪ ታምራት ደጀኔ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በምትፈልገው ጉዳይ ሁሉ ሀገሩን ማገልገል፤ ለሀገሩ ብሔራዊ ጥቅም መቆም ከሁሉም ይጠበቃል።   ሁሉም ሙያ ለሀገሩ ብሔራዊ ጥቅም መቆም እንዳለበት ገልጸው፤ የልህቀት ማዕከሉ ሰልጣኞችም ለዜጎች ተጠቃሚነት ዘብ መቆም አለባቸው ብለዋል፡፡ ጋዜጠኞች ያገኙትን መረጃ ሁሉ ከማሰራጨታቸው በፊት ለሀገር የሚኖረውን ጥቅም ግምት ውስጥ አስገብተው መዘገብ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የባህር በርን ጨምሮ ቀሪ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ስብራቶችን ለመጠገን ከባለድርሻ አካላት ጋር በትጋት እንደሚሰራ ገለጸ
Oct 24, 2025 100
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):- የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የባህር በርን ጨምሮ ቀሪ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ስብራቶችን ለመጠገን ከባለድርሻ አካላት ጋር በትጋት እንደሚሰራ ገለጸ። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮችና የፓርቲ አጀንዳዎች ላይ መክሮ አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጸዋል። ፓርቲው የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና የማረጋገጥ ራዕይን ሰንቆ ወደ ተግባር መግባቱን አውስተው፤ ባለፉት ዓመታት ለህዝብ ቃል የገባውን በውጤታማነት እየፈጸመ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን ቀሪ ስብራቶች ለመጠገን ከባለድርሻ አካላት ጋር በትጋት እንደሚሰራ ተናግረው፤ ብሔራዊ ጥቅምን ማዕከል ያደረጉ የተሟላ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንደሚወጣ ገልፀዋል። በኢኮኖሚው ዘርፍ ባለፉት ዓመታት በተሠሩ የልማት ስራዎች ከፍተኛ ውጤት መምጣቱን ገልጸው፤ ለአብነትም ባለፈው ዓመት የ9 ነጥብ 2 በመቶ እድገት መመዝገቡን ተናግረዋል። የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር እየተረጋገጠ መሆኑን ሥራ አስፈጻሚው መገምገሙን ጠቅሰው፤ በዚህም ኢኮኖሚው ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪና ዘመናዊ አገልግሎት እየተሸጋገረ ይገኛል ብለዋል። በገቢ ማሰባሰብ፣ በወጭ ንግድ እና በተኪ ምርት አመርቂ ውጤት መመዝገቡን በማንሳት አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱ ፈጣን ብቻ ሳይሆን አካታች፣ ጥራት ያለውና የህዝቡን ኑሮ በተጨባጭ እያሻሻለ መሆኑን ጠቅሰዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን በተጀመሩ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸው፤ በሰው ተኮር ስራዎችም በርካታ አቅመ ደካማ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። በቀጣይም ተረጂነትን የማስወገድ፣ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለማሟላት በቂ ፈንድ የመያዝ እንዲሁም ብሄራዊ የመጠባበቂያ ክምችትን በራስ አቅም የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የሰላም እና የፖለቲካ ጉዳዮችን መገምገሙን በማንሳት ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የበኩሉን ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆኑን ማረጋገጡን ጠቅሰዋል። መጪው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተአማኒ፣ ግልጽና አሳታፊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ ፓርቲው የድርሻውን እንደሚወጣም ገልጸዋል። ውስን የሰላምና ፀጥታ ችግር የነበረባቸውን አካባቢዎችን ለማረጋጋት መንግስትና ህዝብ በጋራ በሰሩት ስራ ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። ማንኛውም የፖለቲካ ጥያቄ ያለው አካል ጥያቄውን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ምህዳር መፈጠሩን ገልጸው፤ ፓርቲውና የሚመራው መንግስት ሁልጊዜም በራቸው ለሰላም ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል። በስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ስብሰባው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ የተቀመጠው አቅጣጫ ወደ ተጨባጭ ተግባር መገባቱን ተገምግሟል ብለዋል። በዚህም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማስፋትና የዲጂታላይዜሽን ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን አመልክተው፤ እስካሁንም 16 ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት እየሠጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በመሶብ ማዕከላት የህዝቡ እርካታ ወደ 95 መቶ መድረሱን ገልጸው፤ የመሶብ ማዕከላትን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓም ወደ መቶ ለማድረስ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አቅጣጫ ማስቀመጡን ተናግረዋል። ብልፅግና ፓርቲ ጠንካራ መንግስትና ሀገር ለመገንባት የያዘውን ግብ ለማሳካት የአመራርና አባላቱን አቅም የሚያጎለብቱ የተለያዩ ተግባራትን ማከናወኑንም ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ አመራርና አባላቱ በተሠጣቸው ተልዕኮ ልክ በየደረጃው የመገምገም ስራ ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፤ በምዘናው መሠረት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡት እውቅና መሰጠቱን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የተሰጣቸውን ሀገራዊና የፓርቲ ተልዕኮ በአግባቡ ባልተወጡ አመራሮች ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን መወሰዱን ተናግረው፤ ፓርቲው ህዝብና ሀገርን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራችውን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው 11ኛው የጣና ፎረም በስኬት መጠናቀቅ የክልሉ ከተሞች አህጉራዊና ዓለም አቀፍዊ መድረኮችን በብቃት የማስተናገድ አቅም ያሳየ ነው
Oct 24, 2025 113
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦ በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው 11ኛው የጣና ፎረም በስኬት መጠናቀቅ የክልሉ ከተሞች አህጉራዊና ዓለም አቀፍዊ መድረኮችን በብቃት የማስተናገድ አቅም ያሳየ መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ(ዶ/ር) ገለጹ። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው መድረክ ተጠናቋል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እንዲሁም የአፍሪካ ሀገራት፣ የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተማ በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ(ዶ/ር)፤ በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው 11ኛውን የጣና ፎረም ጉባኤ አስክመልክቶ ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥተዋል። የፎረሙ አስተባባሪ ኮሚቴ በአዲስ አበባና ባሕር ዳር ከተማ ለማካሄድ ውሳኔ ካሳለፈበት ጊዜ ጀምሮ በክልል ደረጃ ኮሚቴ በማደራጀት ውጤታማ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኅይል ኮሚቴም ከፎረሙ ዋዜማ ጀምሮ በዕቅድ የተመራ ዝግጅት በማድረግ የተሳካ ስራ መስራቱንም ተናግረዋል። በዚህም በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደው ፎረም በተደረገው ዝግጅት ልክ በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል። የጣና ፎረም የባሕር ዳር ከተማ ተሳታፊ እንግዶችን ከአቀባበል ጀምሮ አጠቃላይ ሂደት ደስተኞች እንዲሆኑ ለማድረግ በትጋት ሲሰራ መቆየቱን አመልክተዋል። 11ኛው የጣና ፎረም ስኬት ኃላፊነታቸውን ለተወጡ የፌዴራልና የክልሉ የጸጥታና ደህንነት ግብረ ኃይል፣ እንግዳ ተቀባዩ የባህር ዳር ከተማ ህዝብ እና ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። በባሕርዳር ከተማ በስኬት የተካሄደው አህጉራዊ ፎረም የክልሉ ከተሞች አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ መድረኮችን በብቃት ማስተናገድ እንደሚችሉ ትምህርት የሰጠ መሆኑንም ገልጸዋል።
11ኛው የጣና ፎረም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ያላትን የላቀ አስተዋጽኦ የምታጸናበት ነው-አምባሳደር ነብያት ጌታቸው
Oct 24, 2025 156
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-11ኛው የጣና ፎረም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ያላትን የላቀ አስተዋጽኦ የምታጸናበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለጹ። ከጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣ የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተማ በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የጣና ፎረም በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ጉዳዮች ላይ በመምከር መፍትሔ አመላካች ምክረ ሃሳቦች የሚቀርቡበት አህጉራዊ መድረክ ነው ብለዋል። በፎረሙ ላይ የመንግስት አካላት፣ሚኒስትሮች፣አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ምሁራንና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት መሆኑን ተናግረዋል። "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ መካሄድ የጀመረው የዘንድሮው የጣና ፎረም አፍሪካ በተለዋዋጭ የዓለም ሁኔታ የሚኖራትን ሚና እንደሚዳስስ አንስተዋል። ወቅታዊው የዓለም ሁኔታ የፖለቲካ ፉክክር እየከረረና የባለብዙ ወገን ዓለም አቀፍ ትብብር እየላሉ የመጡበት መሆኑን አስረድተዋል። በጣና ፎረም አፍሪካ ውጥረት በተሞላበት ዓለም አቀፍ ሁኔታ የሰላምና ደኅንነት እንዲሁም ሌሎች አጀንዳዎች ላይ ያሏትን መፍትሔዎች እንደምታራምድ አብራርተዋል። የጣና ፎረም ትኩረት አፍሪካዊ መፍትሔዎች ላይ ነው ያሉት አምባሳደር ነቢያት፥ በዚህም ከአፍሪካውያን የመነጩ የሰላምና ደኅንነት የመፍትሔ ሃሳቦች የሚንሸራሸሩበት መድረክ ነው ብለዋል። በመድረኩም ለአፍሪካውያን የፖሊሲ አውጪዎች ምክረ ሃሳብ የሚሆኑ ሀሳቦች የሚወጡበት መሆኑንም ገልጸዋል። ለ11ኛ ጊዜ በባሕር ዳርና በአዲስ አበባ የሚካሄደው የጣና ፎረም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ያላትን የላቀ አስተዋጽኦ የምታጸናበት መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው።
በዞኑ የልማት ስራዎችን ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የተጠናከረ እርምጃ ይቀጥላል
Oct 24, 2025 99
ደሴ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡-በደቡብ ወሎ ዞን የልማት ስራዎችን ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት በሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የተጠናከረ እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ። የደቡብ ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አሊ ይማም፥በዞኑ ያለውን ወቅታዊ የሰላም ሁኔታ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በዞኑ የሰላምና ልማት ጉዳይ የሁሉም አጀንዳ ሆኖ እየተሰራበት መሆኑን አንስተዋል። አሁን ላይ አስተማማኝ ሰላም መኖሩንና የልማት ስራዎችም ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል። የፅንፈኛ ቡድኑ የጥፋት ተላላኪዎች በተለያዩ አጋጣሚዎች በስውር በመንቀሳቀስ ዘረፋና እገታ ለመፈፀም ሞክረው በሕዝቡ ትብብርና በጸጥታ ኃይሉ ጥብቅ ክትትል እርምጃ የተወሰደባቸው መሆኑን አስታውሰዋል። በመሆኑም አሁን ላይ በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በመፈጠሩ የልማት ስራዎችም ተጠናክረው መቀጠላቸውን አረጋግጠዋል። የፅንፈኛው ቡድን ዓላማው መዝረፍና ሰዎችን ማገት መሆኑን ሕዝቡ በአግባቡ በመረዳቱ የሰላሙ ጠባቂ ሆኖ መቆሙን ተናግረዋል። በዞኑ የልማት ስራዎችን ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት በሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የተጠናከረ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በአዲሱ የዓለም ሥርዓት የአፍሪካን እጣ ፋንታ የሚወስን የተሻለ አቅጣጫ መተለም ይኖርብናል-አቶ አረጋ ከበደ
Oct 24, 2025 142
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦በአዲሱ የዓለም ሥርዓት የአፍሪካን እጣ ፋንታ የሚወስን የተሻለ አቅጣጫ መተለም ይኖርብናል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል።   በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣ የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተማ በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፎረሙን በከፈቱበት ወቅት፥ ፎረሙ ለዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች አህጉራዊ ምክረ ሀሳቦችን በመፍትሄነት ማመላከት የሚያስችል ነው። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስተማማኝ፣የበለጸገና የተረጋጋ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምኅዳር ለመፍጠር ጥረት ማድረግ እንደሚኖርበት ገልጸዋል። በአዲሱ የዓለም ሥርዓት የአፍሪካን እጣ ፋንታ የሚወስን የተሻለ አቅጣጫ መተለም ይኖርብናል ብለዋል።   የጣና ፎረም መድረክ የአፍሪካን የተፈጥሮ ሀብቶች ለአፍሪካዊያን የኢንዱስትሪ፣ የግብርና ትራንስፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ለመጠቀም በሚቻልባቸው መንገዶች የራሱን ድርሻ እንደሚወጣ ገልጸዋል። የአፍሪካ ወጣቶችን ፈጣንና ተለዋዋጭ የዓለም ጂኦፖለቲካ የቴክኖሎጂ ጥበባዊ የተጠቃሚነት አሰላለፍ ለመፍጠር መልካም አጋጣሚ መሆኑን አንስተዋል። የጣና ፎረም በባሕር ዳር እንዲካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩ የፌደራልና የክልል እንዲሁም አህጉራዊ ተባባሪ ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው። በፎረሙ ላይ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች ምክክር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በጉጂ ዞን የሰፈነው ሰላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ አግዟል-የጉጂ አባ ገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች
Oct 24, 2025 136
አዶላ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦በጉጂ ዞን የሰፈነው ሰላም የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ ማስቻሉን የጉጂ አባ ገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ፡፡ በዞኑ የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ ታጣቂዎች የተሀድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸው ተመልክቷል፡፡ የጉጂ ሆኩ አባገዳ ገናሌ አጋ በአካባቢው ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን አልምቶ ለመጠቀምና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ አለመግባባቶችን በውይይት መፍታት ይገባል ብለዋል። በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የተሳሳተ መንገድ የተከተሉ ወገኖች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመጡ መንግስት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ በዚህም በአካባቢያቸው በርካታ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪውን በመቀበል ሰርቶ ለመለወጥ ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውን ነው የገለጹት፡፡ ይህም የአካባቢውን ሰላም በማጠናከር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የጉጂ አባገዳ አባል ኡዴሳ አጋ በበኩላቸው፥ ቂምና በቀልን ትተን በመቻቻልና በመረዳዳት ለሀገር ሰላምና ልማት በጋራ ቆመን ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ ለዚህም በአካባቢያቸው ለህብረተሰቡ የሰላምን ዋጋ በማስተማርና የታጠቁ አካላትም የሰላምን መንገድ በመምረጥ ወገኖቻቸውን በልማት እንዲክሱ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። በመንግስት የጸጥታ አካላትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ ሰላምና መረጋጋት እየተጠናከረ መምጣቱ የአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እየተሳለጠ መምጣቱን አንስተዋል፡፡ የመንግስትን የሰላም ጥሪና የአባቶችን ምክር ተቀብለው ወደህብረተሰቡ የተቀላቀሉ ታጣቂዎችም ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ ሌላው አባገዳና የሀገር ሽማግሌ አኖሌ ኖቶ በአካባቢው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንና ልማት እንዲፋጠን የበኩላቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአካባቢውን ማህበረሰብ በሰላም አስፈላጊነትና ችግሮችን በውይይት መፍታት ላይ ከማስተማር ጀምሮ ለዘላቂ ሰላም ከመንግስት ጋር በመቀራረብ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግርዋል። የዞኑ አስተዳደርና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ቦጌ ታፈሰ በበኩላቸው፥ መንግስት አለመግባባቶች በውይይት እንዲፈቱ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ሲያደርግ እንደነበረና ዛሬም ማስቀጠሉን አስታውሰዋል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን አባገዳዎች፣የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የዞኑን ህዝብ ያሳተፈ የሰላም ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም የመንግስትን የሰላም አማራጭ የተቀበሉ ከ200 በላይ ታጣቂዎችና ዘጠኝ አመራሮቻቸው የታሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውን ገልጸዋል። በቅርቡም የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ ሌሎች ታጣቂዎች የበደሉትን ህዝብ ለመካስ የተሀድሶ ስልጠና በመውሰድ ላይ መሆናቸውን ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት በዞኑ ሰላምና መረጋጋት በመፈጠሩ ሁለንተናዊ የልማትና የማህበራዊ እንቅስቃሴ በመፋጠን ላይ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ማህበራዊ
የመማር ማስተማር ሂደትን የተሳለጠ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ሊጠናከር ይገባል 
Oct 24, 2025 65
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ተማሪዎችን በሥነ ምግባር ለማነጽና የመማር ማስተማር ሂደትን የተሳለጠ ለማድረግ የባለድርሻ አካላትን ትብብርና ቅንጅት የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ገለጹ። በትምህርት ቤቶች አካባቢ አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል በወጣ ረቂቅ ደንብ ላይ ባለድርሻ አካላት ውይይት አድርገዋል።   ረቂቅ ደንቡ የአጠቃላይ ትምህርት አዋጁን ለማስፈጸም የወጣ ሲሆን፤ በትምህርት ቤቶች አካባቢ ያሉ አዋኪ ድርጊቶችን በተቀናጀ ግብረ-ሃይል መከላከልን ታሳቢ አድርጓል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ እንዳሉት፤ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማሳለጥ ትምህርትን የሚያውኩ ጉዳዮችን አስቀድሞ መከላከል ያስፈልጋል። የልጆቻችን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወሰነው በትምህርት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ የመማር ማስተማሩን ሂደት የሚያውኩ ተግባራትን መከላከል የጋራ ሃላፊነት መሆኑን አንስተዋል። መንግስት ትምህርት ለአገራዊ ልማትና ብልጽግና ያለውን ቁልፍ ሚና በመረዳት ለትምህርት ጥራትና ተደራሽነት በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ለአብነትን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲውን በሙሉ አቅም ማስተግበር የሚያስችል የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ መውጣቱን አስታውሰዋል። በትምህርት ቤቶች አካባቢ ያሉ አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል የወጣው ረቂቅ ደንብም አዋጁን ለማስፈጸም የሚያስችል ነው ብለዋል። ረቂቅ ደንቡ መልካም ሰብዕና የተላበሰ ዜጋ በማፍራት ለትምህርት ጥራት የራሱን ሚና ይጫወታል ብለዋል። ረቂቅ ደንቡን ለማዳበር የባለድርሻ አካላት ግብዓት ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፤ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማሳለጥና በስነ-ምግባር የታነጸ ዜጋ ለማፍራት የሁሉንም አካላት ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ታደሰ ጌጡ ፤ የደንቡ መውጣት ተማሪዎችን በሥነ ምግባር ለማነጽና የመማር ማስተማሩን ሂደት ማሳለጥ ያስችላል ብለዋል።   በረቂቅ ደንቡ ለመልካም ሥነ-ምግባር ተቃራኒ የሆኑ ጉዳዮች በዝርዝር ሊቀመጡ እንደሚገባ አንስተዋል። የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አበበ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በትምህርት ቤት አካባቢ የሚፈጠሩ አዋኪ ድርጊቶች ዘርፈ ብዙ ናቸው።   ተማሪዎች ከቤት ወጥተው ትምህርት ቤት እስኪገቡ በአካባቢያቸው አዋኪ ጉዳዮች የሚያጋጥማቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዳይከታተሉ ማድረጉንም ነው ያነሱት። በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካሪ የሺወርቅ አያና፤ በትምህርት ቤቶች አካባቢ አዋኪ ድርጊቶችን የመከላከል የሁሉም ኃላፊነት በመሆኑ የደንቡ መውጣት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።   ሚኒስቴሩ የአምስት ዓመት የወጣቶች ሰብዕና ግንባታ ስትራቴጂ እያዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው፤ የረቂቅ ደንቡ መዘጋጀት ለዚህ አጋዥ ይሆናል ብለዋል። በትምህርት ቤቶች አካባቢ አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል የወጣው ደንብ በየደረጃው ያሉ ባለደርሻ አካላት እየተወያዩበት ሲሆን፤ ለፍትህ ሚኒስቴርና ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ይሁንታ ካገኘ በዚህ ዓመት ጸድቆ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ ለመስጠት በሚከናወኑ ተግባራት የበኩሉን ሚና እየተወጣ ነው
Oct 24, 2025 84
ባህር ዳር ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ ለመስጠት በትብብር በሚያከናውኑት ተግባራት የድርሻውን ሚና እየተወጣ መሆኑን አስታወቀ። ከ11ኛው የጣና ፎረም ጎን ለጎን የአፍሪካ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዚዳንቶች የተሳተፉበት መድረክ በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ተካሄዷል።   የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት መንገሻ አየን (ዶ/ር) እንደገለጹት የአፍሪካ ዩኒቨርስቲዎች ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሏቸውን ስራዎች በትብብር እየከናወኑ ይገኛሉ። በዚህ ረገድ ዩኒቨርሲቲው ከሌሎች የአፍሪካ ዩኒቨርስቲዎች ጋር በመተባበር ትላልቅ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚሁ ጎን ለጎን ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ተማሪዎችን በመቀበል ስልጠና እየሰጠ መሆኑንም ለአብነት ጠቅሰዋል ።   የአፍሪካ ዩኒቨርስቲዎች ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ ለማበጀት በሚከናወኑ ተግባራት የተጣለባቸውን ሀላፊነት ለመወጣት አካባቢያዊ እውቀትን በመጠቀም ችግሮችን በራስ አቅም ለመፍታት የሚያስችላቸውን ተግባራት እያከናወኑ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። መድረኩም አፍሪካ እንደ አህጉር፣ ኢትዮጵያ እንደ ሃገር ያላትን እውቀት ከመጠቀም አንፃር አይነተኛ ሚና ለመወጣት እድል እየፈጠረ መሆኑን ጠቁመው ትስስሩን ከመምራትና እንደ አህጉር የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ከማስቀጠል አንጻር ውጤታማ ስራ እንደሚከናወን አመላክተዋል ። በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው መድረክ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌን ጨምሮ ከሱዳን፣ ከሱማሊያና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ፕሬዚዳንቶችና የባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ምሁራን ተሳትፈዋል።
ዘመናዊ የጥበብ ማሳያዎቹ በኪነ ጥበብ ዘርፍ  አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ለማቅረብ ተጨማሪ አቅም  ሆነዋል
Oct 24, 2025 78
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-በመዲናዋ የተገነቡና ዕድሳት የተደረገላቸው ዘመናዊ የጥበብ ማሳያዎች አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ለኢንዱስትሪው ዕድገት ተጨማሪ አቅም የፈጠሩ መሆናቸውን የተለያዩ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ገለጹ። በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል መታሰቢያ የተገነቡ የጥበብ ማሳያዎች፣ የህጻናትና ወጣቶች ቴአትር ኮምፕሌክስ እንዲሁም አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸው ይታወቃል።   በከተማዋ አዲስ የተገነቡና ዕድሳት የተደረገላቸው ነባር ሲኒማና ቴአትር ቤቶች ለከተማዋ ነዋሪዎች አማራጭ የመዝናኛ ስፍራ ከመሆን ባለፈ ለኪነጥበብ ባለሙያዎች ምቹ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር የሚያስችሉ ናቸው።   የቴአትር ደራሲና ባለሙያዋ አለም ፀሐይ እጅጉ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ በከተማዋ አዲስ የተገነቡና እድሳት የተደረገላቸው ዘመናዊ የጥበብ ማሳያዎች የባለሙያዎችን የፈጠራ ችሎታ በማዳበር ለኪነ-ጥበብ ኢንዱስትሪው መነቃቃት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።   የጥበብ ማሳያ መድረኮቹ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የኢትዮጵያን ባህልና እሴት የሚያንፀባርቁና አብሮነትን የሚያጎለብቱ የጥበብ ሥራዎችን በስፋት እንዲሰሩ ያግዛል ነው ያሉት። ኮምፕሌክሶቹ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አገር በቀል ትውፊትን የሚያሳዩ የጥበብ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያስችሉ መሆናቸውን የገለጹት የቴአትር አዘጋጅ የሆኑት ራሔል ተሾመ ናቸው።   የኪነ ጥበብ እድገት በባለሙያው የሚወሰን በመሆኑ የዘርፉ ተዋናዮች ስራቸውን የሚያሳዩበት ቦታ ደረጃውን የጠበቀ መሆኑ በቀጣይ ለሚሰሩ ስራዎች መነቃቃት የሚፈጥር ነው ብለዋል። የኬሮግራፊ ወይም የውዝዋዜ ባለሙያ የሆነው ጌታሁን ስሜ፤ ቀደም ሲል የነበሩ ሲኒማና ቴአትር ቤቶች ውስንነት የነበረባቸው ፣የጥበብ ስራን ለማቅረብ የማይመቹና ፣የባለሙያውንና የህዝቡን ፍላጎት የማያሟሉ እንደነበሩ አስታውሷል፡፡   አዲስ የተገነቡት የጥበብ ማሳያ ስፍራዎች አለም አቀፍ የፊልም አውደ ርዕይን ጨምሮ ታላላቅ የኪነ ጥበብ ስራዎችን ማስተናገድ የሚችሉ መሆናቸውን ገልጿል። የቴአትርና የፊልም ባለሙያው ተስፉ ብርሃኔ በበኩሉ፤ ሲኒማ ቤቶቹ ለተመልካች ብቻ ሳይሆን ለኪነ ጥበብ ባለሙያዎች አመቺ ምህዳር የፈጠሩ ናቸው ብሏል።   የቴአትር ጥበብ ባለሙያ እና መምህር እዮብ ገረመው እንዳሳሰቡት፤ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የህዝቡን የእርስ በርስ ግንኙነት የሚያጠናክሩ ስራዎች መስራት ይጠበቅባቸዋል።   ሲኒማ እና ቴአትር ቤቶቹ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ለመስራት መነሳሳትን የሚፈጥሩ መሆናቸውን የተናገረው የቴአትርና የፊልም ባለሙያው ተስፉ ብርሃኔ ነው። የኬሮግራፊ ባለሙያው ጌታሁን ስሜ በበኩሉ የህዝብን አንድነትና ሰላም የሚያረጋግጡ የጥበብ ስራዎችን መስራት የዘወትር ተግባራችን ሊሆን ይገባል ብሏል።
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ለተማሪዎች ምገባና ለግብዓት አቅርቦት ትኩረት ተሰጥቷል  
Oct 24, 2025 109
ኮምቦልቻ/ጎንደር ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-በአማራ ክልል የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ለተማሪዎች ምገባና ለግብዓት አቅርቦት ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ። ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያውን የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም መድረክ በደሴና በጎንደር ከተሞች እያካሄደ ነው።   የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መኳንንት አደመ በኮምቦልቻ ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ እንደገለጹት፣ በክልሉ የትምህርት ተደራሽነትንና ጥራትን ለማስጠበቅ ለተማሪዎች ምገባ፣ ለግብዓት አቅርቦትና ትምህርት ቤቶቹን ለመማር ማስተማር ሥራው ምቹ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቷል።   የመማር ማስተማር ሥራውን ውጤታማ ከማድረግ ባለፈ የጸጥታ ችግር ተከስቶ በነበረባቸው አካባቢዎችም ትምህርቱን ለማስቀጠል ከማህበረሰቡ ጋር መሰራቱን ገልጸዋል። ከግብአት አቅርቦት ጋር በተያያዘ በመማሪያ መጻህፍት ላይ የሚስተዋለውን እጥረት ለማቃለል የመጻህፍት ህትመት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። የመማር ማስተማር ስራውን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የምሁራን፣ የሐይማኖት አባቶች፣ የሐገር ሽማግሌዎችና የወላጆች ተሳተፎን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱንም አቶ መኳንንት አክለዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለምነው አበራ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በትምህርት ዘመኑ ከ458 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ።   በተመሳሳይ በጎንደር ከተማ በተካሄደ መድረክ ላይ የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ደምስ እንድሪስ እንደገለጹት በክልሉ በትምህርት ዘመኑ 3 ነጥብ 8 ሚሊዮን ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ መጥተዋል።   ለዚህ ውጤት የትምህርት አመራሩ፣ የወላጆች፣ የመምህራን፣ የክልሉ መንግስትና ህብረተሰቡ በቅንጅት መስራታቸው የጎላ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው በበኩላቸው በእውቀትና በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ እድገት ለማስመዝገብ ትውልድ ላይ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡   ለዚህም የከተማ አስተዳደሩ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ከ132 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታ ለማምጣት አቅዶ አብዛኛውን ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል። ልጆች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆን የለባቸውም በሚል ቁጭት ወላጆች ቁርጠኛ አቋም ወስደው እየሰሩ ነው ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ሃላፊ አቶ ክንዱ ዘውዱ ናቸው፡፡   በዚህም በዘንድሮ የትምህርት ዘመን ከ500 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመመዝገብ ወደትምህርት ገበታ ለማምጣት ተችሏል ብለዋል። ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው መድረክ ከአማራ ክልልና ከክልሉ የተለያዩ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ የዘርፉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ ዕድገት አይቀሬ መሆኑን አመላካች አፈጻጸሞች ተመዝግበዋል
Oct 24, 2025 84
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡- በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ አፈጻጸሞች ስኬታማነት የኢትዮጵያን ብልጽግና አይቀሬነት አመላካች መሆናቸውን ሚኒስትሮች ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ ከሚኒስትሮች ጋር በመሆን በኮይሻ ግድብ አካሂደዋል። ከግምገማው ጎን ለጎንም ኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን ጨምሮ ጨበራ ጩርጩራ የዝሆኖች ዳና ሎጂን ጎብኝተዋል።   በዚሁ ወቅት የሥራና ክኅሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በሰጡት አስተያየት፤ መሪነት ያለንን ዐውቀንና ፀጋችንን ለይተን ወደ ሀብትነት መቀየርን ይፈልጋል ብለዋል። ከዚህ አንጻር ጨበራ ጩርጩራን በማልማት ወደ ሀብትነት የመቀየር ሥራ መሠራቱን ጠቅሰው፤ ይህም አካባቢውን በማስተሳሰር እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል ሲሉ ገልጸዋል። ከፍ ሲልም በቱሪዝሙ ዘርፍ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት አመላክተው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመሪነት ጥበብን ተጠቅመው ካለን በመጀመር መርኅ እየሠሩ መሆናቸውን ያሳያል ነው ያሉት።   ከ100 ቀናት አፈጻጸም ጋር በተያያዘ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በሰጡት አስተያየት ደግሞ፤ በሁሉም መስኮች ተስፋ የሚፈነጥቁ አፈጻጸሞች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። የግብርናው ዕድገት ከሌሎች ዘርፎች ዕድገት ጋር ተሳስሮ በመሠራቱ ተስፋችንን መጨበጥ ጀምረናል ብለዋል። የሕዳሴው ግድብ፣ የወልመል መስኖ፣ የማዳበሪ ፋብሪካ እና ሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶች ተስፋችንን መጨበጥ መጀመራችንን ብሎም የኢትዮጵያ ብልጽግና አይቀሬነት አመላካች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል። አፈጻጸሙ እንደሚያስረዳው የተቀመጡ ግቦች በስኬት እየተከናወኑ ነው፤ የግብርናው ዕድገትም በአርሶና አርብቶ አደሩ ኑሮ ሁሉ የሚገለጥ ሆኗል ነው ያሉት። የተመዘገቡት ውጤቶች የተገኙት በፈተና ውስጥ መሆኑ ደግሞ ሀገራችንን ፈተና ሳይበግራት ስኬታማ ጉዞ ማድረግ መቻሏን እንደሚያሳይ አንስተዋል። አዲስ የሥራ ባህል እየተፈጠረ መሆኑን ዐይቻለሁ ያሉት ሚኒስትሩ፤ ሕዝብን በማሳተፍ ጀምሮ የመጨረስ ዐቅም እያደገ መምጣቱንም ታዝቤያለሁ ብለዋል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ስለኮይሻ እና ጨበራ ጩርጩራ በሰጡት ሐሳብ፤ ካለፈው ዓመት አንጻር ሥራው እያደገ መሆኑን ተመልክቻለሁ ነው ያሉት። አዳዲስ መዳረሻዎች ተገንብተው ለኢኮኖሚ ማመንጨት ተደማሪ ዐቅም እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ የነበራትን ፀጋ ለይቶ እና ዐውቆ ወደ ሀብት መቀየር ጊዜ ይፈልግ ነበር፤ አሁን ጊዜው ሆኖ ወደ ሀብት እንዲቀየሩ እየተደረገ ነው ሲሉም አመላክተዋል። አሁን ላይ የቱሪዝም ሀብት እየሰፋ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በግንባታ ላይ የሚገኙት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ የሰው ልጅ ሊጎበኛቸው የሚገባ መዳረሻዎች እንደሚሆኑም ተናግረዋል። ሀገር ያላትን ዐቅምና ፀጋ በመለየት እየተከናወኑ ባሉ አዳዲስ መዳረሻዎች እና በ100 ቀናት አፈጻጸም በሁሉም ዘርፍ ለተገኙ ስኬቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ሚኒስትሮቹ ገልጸዋል።
የኮይሻ ግድብ የለውጡ መንግስት እንደ ሕዳሴ ግድብ የታደገው ፕሮጀክት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Oct 24, 2025 68
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):- የኮይሻ ግድብ የለውጡ መንግስት እንደ ሕዳሴ ግድብ ከታደጋቸው ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማን አስመልክቶ በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት በሰጡት አስተያየት ከዓመታት በፊት የኮይሻ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ መሰረት ከመጣል ባለፈ አፈጻጸሙ በሚፈለገው ደረጃ ላይ እንዳልነበር ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ያለበት የግንባታ ደረጃ ከዚህ ቀደም ከነበረው ከፍተኛ ለውጥ እንዳለው አመልክተዋል። የኮይሻ ግድብ ከኤሌክትሪክ ማመንጨት ባሻገር ለቱሪዝም መስህብነት የሚሆኑ ስራዎች እንደተካተቱ ጠቁመው፤ ሎጆችን ጨምሮ የተለያዩ ግንባታዎችን ማከናወን የሚያስችሉ ተራራዎች እንዳሉ አንስተዋል። የግንባታው ስራ በፍጥነት እየሄደ መሆኑን ጠቅሰው፤ ግድቡ 1ሺህ 800 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።   ኮይሻ ለየት ያሉ በርካታ ተራሮች የሚገኙበትና ትልቁ የኦሞ ወንዝ የሚፈስበት መሆኑን ገልጸው፤ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋ ከተጠቀመች የሚፈለገውን ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል የሚያሳይ እንደሆነም ነው የገለጹት። ኮይሻ ግድብ የለውጡ መንግስት እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከታደጋቸው ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑንም ነው የተናገሩት። ኮይሻ፣ ሃላላ ኬላ እና ጨበራ ጩርጩራ ፓርክ ከኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቱ ጋር ተዳምረው ቱሪዝሙን ማሳደግ የሚችሉ ጸጋዎች መሆናቸውንም አመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለኮይሻ ግድብ ግንባታ መፋጠን ለሰጡት በሳል አመራርም አመስግነዋል።
ኢትዮጵያ ትበለጽጋለች የሚገባትንም ስፍራ ትይዛለች -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 24, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞዋን በማሳካት የሚገባትንም ስፍራ ትይዛለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማን አስመልክቶ በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በለውጡ ዓመታት ትኩረት ከተሰጣቸው ስራዎች መካከል አንዱ ኢትዮጵያንና ጸጋዎቿን በሚገባ ማወቅ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ብቃት እና አቅም በቅጡ መገንዘብ ሀገርን ለመስራት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ጠቅሰው፤ በዚህ ሂደት ውስጥ በርካታ አቅምን የሚገልጡ ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል።   የጨበራ ጩርጩራ ፓርክ እና ኮይሻ የሀገርን አቅም የገለጡና ውጤት የተገኘባቸው ስራዎች መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። ሀገሩን የሚያውቅ እና በሀገሩ ክብር የሚሰማው ሰው ተግቶ ለመስራት እና እያንዳንዷን ቀን ለመለወጥ እድል አድርጎ እንዲወስድ እድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት ያየነቻው ፈተናዎችና መከራዎች አጠንክረውን በበለጠ ጽናት ተግተን እንድንስራ እና ውጤት እንድናገኝ አድርገውናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ኢትዮጵያ እንደምትበለጽግና የሚገባትን ስፍራ እንደምትይዝ ምንም ጥርጥር የለውም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህን ራዕይ ለማሳካት የእያንዳንዱን ዜጋ ጥረት እና ድካም እንደሚጠይቅ አመልክተዋል። ተግተን ከሰራን በልጆቻችን ላይ ፍሬውን ለማየት ጊዜው ሩቅ አይደለም ሲሉም ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሶስት ወራት በሁሉም መስኮች ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰው፤ በአንዳንድ መስኮች የተገኘው ውጤት ከተጠበቀው በላይ መሆኑንም አመልክተዋል። የተገኙ ውጤቶች በቀጣይ የሩብ ዓመታት በማስቀጠል ውጤቶችን ማላቅ ከተቻለ የኢትዮጵያን የኃይል ሽግሽግ የሚቀይሩ መሰረታዊ ጉዳዮች የሚከናወኑበት ዓመት እንደሚሆንም ተናግረዋል። የተገኙ ውጤቶችን ለማጽናት በበለጠ ትጋት እና አቅም መስራት እንደሚገባም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አሳስበዋል።
''ጉዞ ወደ ሀገር ቤት''  የሚል የጉብኝት መርሃ-ግብር ሊካሔድ ነው
Oct 24, 2025 125
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ኢትዮጵያን ለማስተዋወቅ፣ ብዝሃ ሀብቷን ለማሳየትና ብሄራዊ ኩራትን ለማጎልበት እድል የሚፈጥር ''ጉዞ ወደ ሀገር ቤት'' የሚል መርሃ ግብር ሊካሄድ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ገለጹ። መርሀ ግብሩ ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሔድ ስለመሆኑም ተገልጿል። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ሀገራዊ የጉብኝት መርሃ ግብሩን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ''ጉዞ ወደ ሀገር ቤት'' ከኢትዮጵያ ወደ ተለያዩ ዓለም ሀገራት በጉዲፈቻ የሄዱ ህጻናት ሀገራቸውን ባህላቸውንና ማንነታቸውን እንዲያውቁ ታልሞ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   በተጨማሪም ከሀገራቸው ጋር ያላቸውን ትስስር እንዲያጠናክሩና ቀጣይነት ያለው ግንኙነትን ለመፍጠር የሚያግዝ ስለመሆኑም አብራርተዋል። ይሄው ለሰባት ቀናት የሚካሔደው የጉብኝት መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ያላትን ብዝሃ ሀብት ለማስተዋወቅና ብሄራዊ ኩራትን ለማጎልበት እድል የሚፈጥር ነውም ብለዋል። በተጨማሪም የውጭ ጎብኝዎችን ለመሳብ እና አማራጭ የጉብኝት መርሃ ግብርን ለማዘጋጀት ዓይነተኛ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍፁም አረጋ በበኩላቸው፤ መርሀ ግብሩ በጉዲፈቻ ባህር ማዶ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ያላቸው የህይወት ጥያቄ መልስ የሚያገኙበትን እድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።   አገልግሎቱ በተለይ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በቱሪዝም፣ በንግድና በኢንቨስትመንት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑንም ገልፀዋል።   የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽነር ሁንዴ ከበደ፤ ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በመዲናዋ የሚገኙ የተመረጡ የቱሪዝም መስህቦችን በማስጎብኘት በኩል ዝግጅት መደረጉን ገልፀዋል።እንግዶች ያማረ ቆይታ እንዲኖራቸው እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የአህጉሪቱን ወጣቶች የፈጠራ አቅም  ማጎልበት ይገባል - ምክትል ሊቀ-መንበር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ
Oct 22, 2025 247
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ):- የበለፀገች አፍሪካን ለመገንባት ቴክኖሎጂና ፈጠራን ከአጀንዳ 2063 ጋር ማቀናጀትና የወጣቶችን የፈጠራ አቅም ማጎልበት እንደሚገባ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት የኢኖቬሽን ፌስቲቫል በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል፡፡   ፌስቲቫሉ "የአፍሪካ ህብረት ወጣቶችን የአህጉራዊ ኢኖቬሽን መሪ የማድረግ ተግባር" በሚል ርዕሰ ጉዳይ የሚካሄድ ሲሆን ኢኖቬተሮች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የግሉ ዘርፍ መሪዎች እና የወጣት ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ፌስቲቫሉ ለሀገር በቀል የኢኖቬሽን መፍትሄዎች እውቅና በመስጠት ስራዎችን የበለጠ ማላቅ ላይ ትኩረት የሚያደርግ መሆኑ ተመላክቷል። የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ ፈጠራንና ቴክኖሎጂን ከአጀንዳ 2063 ጋር በማቀናጀት የበለፀገች አፍሪካን ለመገንባት መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡   አፍሪካን ለመለወጥና ለማሳደግ ብሎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን ፈጠራን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የአህጉሪቱ የፈጠራ ችሎታ፣ የዲጂታል ለውጥ እና የሥራ ፈጠራ ዋና አንቀሳቃሽ ኃይሎች ወጣቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ አህጉሪቱ በፈጠራ ዘርፍ የያዘችውን ግብ ማሳካት የሚችሉት ወጣቶች በመሆናቸው አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግላቸው ይገባል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የሴቶች፣ የጾታ እና ወጣቶች ዳይሬክተር ፕሩደንስ ንግዌንያ በበኩላቸው ወጣቶችና ሴቶች የአፍሪካን የፈጠራ ምህዳር መሠረት መጣል ይገባቸዋል ብለዋል፡፡   አፍሪካ በፈጠራ ዘርፍ ማሳካት የምትፈልገውን ለውጥ እውን ለማድረግ በወጣቶችና ሴቶች የፈጠራ አቅም ላይ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ የፌስቲቫሉ ተሳታፊ ወጣት ትመር ብርሃኔ አፍሪካዊያን በቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ዘርፍ ያለንን ዕውቀት በየጊዜው ማላቅ አለብን ስትል ተናግራለች፡፡   ወጣት አሜን ቢኒያም በበኩሏ የምንፈልጋትን አፍሪካ እውን ለማድረግ ፈጠራን እና ቴክኖሎጂን ማሳደግ ተገቢ መሆኑን ጠቅሳ ለዘርፉ የሚደረገውን ድጋፍ በማጠናከር የተያዘው ግብ ስኬታማ ማድረግ የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝባለች፡፡   የኢኖቬሽን ፌስቲቫሉ እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአጀንዳ 2063 ግቦችን ለማሳካት፣ አካታችና ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ ራዕይ አቀጣጣይ እንዲሆን እየተሰራ እንደሚገኝም ተገልጿል፡፡
የማር ጥራት ፍተሻን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ለማካሄድ የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ ነው 
Oct 22, 2025 190
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦የማር ምርትን የጥራት ፍተሻ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ለማካሄድ የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አስታወቀ። ድርጅቱ ፍተሻውን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ አቅም ለማካሄድ ከተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የዓለም አቀፍ ገበያ ተደራሽነት መርሃ ግብር ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑን ገልጿል።   በኢትዮጵያ ከፍተኛ የማር ምርት አቅም ቢኖርም በሚፈለገው ልክ የውጭ ምንዛሬ እየተገኘበት አለመሆኑ የተገለጸ ሲሆን ለዚህ ደግሞ የማር ጥራት ጉዳይ አንዱና ዋነኛው ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የፍተሻ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ምትኩ ድሪባ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የማር ምርት ጥራትን ለማስጠበቅ የጸረ ተባይ ቅሪት ፍተሻ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ አቅም ለማካሄድ ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው።   ለዚህም ከተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት ጋር በመተባበር እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ለፍተሻ የሚያስፈልጉ መሳሪያዎች ዝግጁ መደረጋቸውን አብራርተዋል። ፍተሻውን ለማከናወን ክህሎት ያለው ባለሙያ ያስፈልጋል ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ አሁን ላይ ከውጭ በመጣ አሰልጣኝ ለባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየተሰጠ ነው ብለዋል። ከዚህ ቀደም በማር ላይ የሚገኘውን የጸረ ተባይ ቅሪት ፍተሻ የሚደረገው ናሙና ወደ ውጭ ተልኮ መሆኑን አስታውሰው፤ አሁን ላይ ፍተሻውን ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን አስታውቀዋል።   ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እየሰራች መሆኑን ጠቁመው፤ ተወዳዳሪ ለመሆን መሰል የላብራቶሪ አቅም መገንባቱ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። የውጭ ምንዛሪ በማስቀረት ረገድም ፍተሻው በሀገር ውስጥ መካሄዱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል። በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የምግብና መጠጥ ፍተሻ ላቦራቶሪ ሲኒየር አናሌቲካል ኬሚስት ብሩክ ስለሺ በበኩላቸው፤ የአቅም ግንባታ ስልጠናው በሌሎች ምርቶች ላይም የጸረ ተባይ ቅሪትን መፈተሽ የሚያስችል አቅም ለመገንባት ያስችላል ብለዋል።   በተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የዓለም አቀፍ ገበያ ተደራሽነት መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሰለሞን መንገሻ በመርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የላቦራቶሪ አቅም እንዲገነባ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል።   ለላቦራቶሪ የሚያስፈልጉ የተለያዩ መሳሪያዎች ድጋፍ መደረጉን ገልጸው፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች የሥራ ላይ ስልጠና እንዲሰጡ እየተደረገ ነው ብለዋል። ለማር ምርት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች ተደራሽ መደረጋቸውን የገለጹት አስተባባሪው፤ የተሻለ ተሞክሮ ያላቸው ሀገራት ልምድ ተቀምሮ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለዜጎች  ፈጣን፣ ወጪ ቆጣቢና ፍትሃዊ  አሰራርን ለመዘርጋት ያስችላል - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Oct 22, 2025 166
ጋምቤላ ፤ ጥቅምት 12/ 2018 (ኢዜአ) ፡- መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ወጪ ቆጣቢ አሰራርን በመዘርጋት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። በጋምቤላ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ተጀምሯል።   በዚህ ወቅት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ እንደተናገሩት፤ በክልሉ የታቀደውን ልማትና እድገት በማፋጠን ለሕዝቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋና ዘመናዊ ማድረግ ያስፈልጋል። የተቋማትን አገልግሎት በአንድ ቦታ መስጠት የሚያስችለው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ደግሞ እንግልትን በማስቀረት ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ወጪ ቆጣቢ አሰራርን በመዘርጋት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።   ማዕከሉ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው አንስተው፤ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት ረገድም የጎላ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ለስኬታማነቱ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ (ዶ/ር)፤ እንደ ሀገር የታዩትን የልማት ስኬቶች ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሰው ተኮር የአገልግሎት ልህቀታችንን ልናጎለብት ይገባል ብለዋል።   ታላቁ የኢትዮጵያ ሕድሴ ግድብ ግንባታ፣ የቱሪዝም መስህብ ማዕከላት ፣የከተሞች ኮሪደር ልማት፣ የሌማት ትሩፋትና ሌሎች የልማት ስኬቶች የኢትዮጵያ የማንሰራራት መገለጫ መሆናቸውን አንስተዋል። በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ መሰረታዊ ለውጥ ማስመዝገብ ፈተና ሆኖ መቆየቱን አስታውሰው፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተግባራዊ በማድረግ ሰው ተኮር የአገልግሎት ልህቀትን በመተግብር ለዜጎች ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት ተጀምሯል ብለዋል።   በመሆኑም እንደ ሀገር የብልጽግና ጉዞን እውን ለማድረግ ለዜጎች የሚሰጠውን አገልግሎት ማዘመን ጊዜው የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑን ኮሚሽነሩ ተናግረዋል። በክልሉ ለሕብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት የማዘመኑ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ደግሞ የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ላክዴር ላክባክ ናቸው።   በክልል ደረጃ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በጋምቤላ ከተማ አስተዳደርና በዞን መዋቅሮችም የማስፋት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ኢኖቬሽንን የአፍሪካ ልማት ምሰሶ ለማድረግ የሚያስችሉ አሰራሮች ገቢራዊ እየሆኑ ነው- የአፍሪካ ህብረት
Oct 22, 2025 181
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት ኢኖቬሽን ለአፍሪካ አካታች እና ዘላቂ ልማት አቀጣጣይ ሞተር ለማድረግ የሚያስችሉ አሰራሮችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ አስታወቀ። የአፍሪካ ህብረት የኢኖቬሽን ፌስቲቫል በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል። “የአፍሪካ ህብረት ወጣቶችን የአህጉራዊ ኢኖቬሽን መሪ የማድረግ ተግባር” የፌስቲቫሉ መሪ ሀሳብ ነው። በፌስቲቫሉ ላይ ኢኖቬተሮች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የግሉ ዘርፍ መሪዎች እና የወጣቶች ተወካዮች ይሳተፋሉ። ሁነቱ ለሀገር በቀል የኢኖቬሽን መፍትሄዎች እውቅና በመስጠት ስራዎችን የበለጠ ማላቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የአፍሪካ ብሩህ አዕምሮዎችን ከፋይናንስ አቅርቦት፣ ዘመኑ ከደረሰበት ክህሎት እና እድሎች ጋር በማገናኘት የኢኖቬሽን ስራዎችን የማሳደግ ፋይዳው የጎላ መሆኑም ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቷ ዜጎች የበለጸጉ የኢኖቬሽን መፍትሄዎች ድጋፍ በማድረግ እና ለወጣት መር የኢኖቬሽን ስራዎች ምቹ ምህዳር ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል። በህብረቱ የዲጂታል እና ኢኖቬሽን ፕሮግራም አማካኝነት ከ10 የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ 18 ወጣት ኢኖቬተሮችን በተቋሙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች በማሰማራት ለኦፕሬሽን ፈተናዎች የተጠኑ የዲጂታል መፍትሄዎችን እንዲሰጡ እያደረገ መሆኑን ገልጿል። ፕሮግራሙን የሚደግፍ የአፍሪካ ህብረት የኦኖቬሽን ቤተ ሙከራ በማቋቋም ተቋማዊ የኢኖቬሽን አቅም ለመገንባት እና ትብብርን ለማጠናከር እየተጠቀመ እንደሚገኝም ነው ያስታወቀው። በዜጎች የቴክኖሎጂ ፈንድ አማካኝነትም 15 ኢኖቬተሮች ዜጎች በፖሊሲ ቀረጻ ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ የሚያሳድጉ መፍትሄዎችን እንዲያቀርቡ የፋይናንስ እና ቴክኒክ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። በተጨማሪም የአፍሪካ ህብረት እድሜያቸው ከ15 እስከ 25 የሆኑ ወጣት ሴት ኢኖቬተሮች በአህጉሪቷ ያሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በዲጂታል እና ቴክኖሎጂ አማራጮች እንዲፈቱ የቴክኒክ እና የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበት ኢኒሼቲቭ ገቢራዊ እያደረገ ነው። ይህም የስርዓተ ጾታ አካታችነት መሰረት ያደረገ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን እንዲድጉ የሚያስችል መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ህብረቱ ኢኖቬሽን የአጀንዳ 2063 ግቦችን ለማሳካት እና ሁሉን አካታችና ዘላቂ ልማት የማረጋገጥ ራዕይ አቀጣጣይ እንዲሆን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል። የኢኖቬሽን ፌስቲቫሉ እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ስፖርት
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል 
Oct 24, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018 (ኢዜአ):- የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳምንት ሊድስ ዩናይትድ እና ዌስትሃም ዛሬ በሚያደርጉት ጨዋታ ጅማሮውን ያገኛል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኢላንድ ሮድ ስታዲየም ይካሄዳል። አዲስ አዳጊው ሊድስ ዩናይትድ በስምንት ነጥብ 16ኛ ደረጃን ሲይዝ ዌስትሃም ዩናይትድ በአራት ነጥብ 19ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሊድስ ዘንድሮ በሊጉ ባደረጋቸው ስምንት ጨዋታዎች ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ አራት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። ሁለት ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። በጨዋታዎቹ ሰባት ግቦችን ሲያስቆጥር 13 ጎሎችን አስተናግዷል። ተጋጣሚው ዌስትሃም በሊጉ እስከ አሁን ባከናወናቸው ስምንት ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። ስድስት ጊዜ ሲሸነፍ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። በስምንቱ ጨዋታዎች ስድስት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 18 ግቦች ተቆጥረውበታል። የውጤት ማጣት ቀውስ ውስጥ የሚገኘው ዌስትሃም ግራሃም ፖተርን አሰናብቶ ኑኖ ስፕሪቶ ሳንቶን መሾሙ ይታወቃል። ሁለቱ ክለቦች በፕሪሚየር ሊጉ ሲገናኙ የአሁኑ ለ27ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 26 ጨዋታዎች ሊድስ ዩናይትድ 14 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። ዌስትሃም ሰባት ጊዜ ድል ሲቀናው በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። በጨዋታዎቹ ሊድስ 45፣ ዌስትሃም 32 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ቡድኖቹ ለመጨረሻ ጊዜ በሊጉ የተገናኙት እ.አ.አ በ2023 ሲሆን በወቅቱ ዌስትሃም 3 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የዛሬው ጨዋታ ሶስት ነጥብ በውጤት ማጣት ቀውስ ውስጥ ለሚገኙት ክለቦች ወሳኝ የሚባል ነው። የ43 ዓመቱ ስቱዋርት አትዌል ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳምንት መርሃ ግብር እስከ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
አካባቢ ጥበቃ
በኢትዮጵያ ዘላቂ የሆነ የባዮ ኢነርጂ ልማት እና የታዳሽ ኃይል ልማትን የሚያጠናክሩ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል
Oct 24, 2025 77
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-በኢትዮጵያ ዘላቂ የሆነ የባዮ ኢነርጂ ልማት እና የታዳሽ ኃይል ልማትን የሚያጠናክሩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን አስታወቀ። በኢትዮጵያ ዘላቂ የሆነ የባዮ ኢነርጂ ልማት ለማምረት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተደርጓል።   ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ጌታቸው እና መቀመጫውን እንግሊዝ አገር ያደረገው ሰንበርድ ባዮ-ኢነርጂ አፍሪካ ስራ አስፈፃሚ ሪቻርድ ቤኔት ተፈራርመውታል። ሰንበርድ ባዮ-ኢነርጂ አፍሪካ በአህጉሪቱ ግዙፍ የባዮ-ፊውል አምራች ኩባንያ ነው። ኩባንያው ግብርናን መሰረት ያደረገ የባዮ ኢነርጂ ልማት፤ የአቪዬሽን ነዳጅ፣ ለትራንስፖርት የሚሆን ታዳሽ ኃይል፣ ለምግብ ማብሰያ የሚሆን ባዮ ፊውል ያመርታል ተብሏል። የተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ በታዳሽ ሃይል አማራጭ ላይ የጀመረችውን ስራ የበለጠ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ጌታቸው በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ስምምነቱ ኢትዮጵያ የጀመረችውን ዘላቂ የኢነርጂ ልማት የሚያጠናክር ነው።   ስምምነቱ ከውጪ የሚገባውን ነዳጅ ለመቀነስና የኢነርጂ ደህንነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ የግብርና ልማትን ለማገዝ፣ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪውን የኢነርጂ ፍላጎት በሀገር ውስጥ ምርት ለመሸፈን እገዛ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል። የሰንበርድ ባዮ-ኢነርጂ አፍሪካ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሪቻርድ ቤኔት በበኩላቸው፤ ኩባንያቸው በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ልማት ውጤታማ ተግባር እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።   ድርጅቱ በዛምቢያና ሴራሊዮን በታዳሽ ኢነርጂ ልማት ላይ መሰማራቱን አስታውቀው ያለውን ልምድ በመጠቀም በኢትዮጵያ ውጤታማ ስራ እንደሚያከናውን አረጋግጠዋል። የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አማካሪ አቶ ከድልማግሥት ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ስምምቱ በሀገሪቱ ከብክለት የጸዳ ትራንስፖርት ለመተግበር እየተደረገ የሚገኘውን እንቅስቃሴ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።   ሚኒስቴሩ ከተሽከርካሪዎች የሚለቀቀውን በካይ ጋዝ ለመቀነስ የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለጎርፍ አደጋ መከላከል የምታደርገው ጥረት የጎርፍ አደጋን በዘላቂነት ለመቀነስ ወሳኝ ሚና አለው
Oct 24, 2025 112
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ኢትዮጵያ ለጎርፍ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት የምታደርገው ጥረት የጎርፍ አደጋን በዘላቂነት ለመቀነስ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኦሞ-ጊቤ እና በስምጥ ሸለቆ ተፋሰሶች ውስጥ የሚከሰተውን የጎርፍ አደጋ በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል የተፋሰስ ጥናት (Basin Level Study) ለማካሄድ ኤስ ደብሊው ኤስ (SWS) ከተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) እና የኤስ ደብሊው ኤስ (SWS) ዓለም አቀፍ አማካሪ ድርጅት ባለቤት እና ስራ አስኪያጅ ጃያን ካርሎ ስምምነቱን ተፈራርመዋል። ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)በዚህ ወቅት እንዳሉት፥ ጎርፍ በግብርና ሰብሎች፣ በወሳኝ መሠረተ ልማቶች፣ በሌሎች ንብረቶች እና በሰው ሕይወት ላይ ለሚያደርሰው አደጋ ዘላቂና ሳይንሳዊ መፍትሔ ማበጀት ይገባል፡፡ የጎርፍ አደጋን መከላከል የመንግስት ሀገር አቀፍ የትኩረት መስክ መሆኑን በማንሳት፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚከሰተውን የጎርፍ አደጋ መከላከል የሚያስችል ውጤታማ ስራ ተከናውኗል ብለዋል፡፡ የጎርፍ አደጋን በዘላቂነት ለመከላከል ከዓለም ባንክ ጋር በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬው ስምምነት የኢትዮጵያ የጎርፍ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋገር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኦሞ-ጊቤ እና በስምጥ ሸለቆ ተፋሰሶች ላይ የሚካሄደው የተፋሰስ ደረጃ ጥናት የጎርፍ አደጋን በዘላቂነት ለመቀነስ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረውም ተናግረዋል፡፡ የጥናቱ ዝርዝር ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ወሳኝ ግብዓት የሚሆኑ ጥልቅ ሳይንሳዊ መሰረት ያለው የመፍትሄ ሀሳቦችን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል፡፡ ‎የኤስ ደብሊው ኤስ (SWS) ዓለም አቀፍ አማካሪ ድርጅት ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ጃያን ካርሎ በበኩላቸው፤ የጎርፍ አደጋን መቀነስ የሚያስችል መፍትሔ ለማበጀት ጠንክረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ የኤስ ደብሊው ኤስ (SWS) ዓለም አቀፍ አማካሪ ድርጅት ጥናቱን በአንድ ዓመት ውስጥ እንደሚያጠናቀቅ ተገልጿል፡፡
ሐረር ከተማን ከፕላስቲክ ቆሻሻ ነፃ ለማድረግ የተጀመረው ኢንሼቲቭ ዓለም አቀፍ ዕውቅና አገኘ
Oct 23, 2025 212
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 13/2018(ኢዜአ)፡- ሐረር ከተማን ከፕላስቲክ ቆሻሻ ነፃ ለማድረግ የተጀመረው ኢንሼቲቭ በዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ዓለም አቀፍ ዕውቅና አግኝቷል። ዕውቅናው የተሰጠው ከኪዩቢክ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ሐረር ከተማን ከፕላስቲክ ነፃ ለማድረግ በተጀመረው የተቀናጀ አሠራር ለተገኘው ውጤት መሆኑን የሐረሪ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ሔኖክ ሙሉነህ ለኢዜአ ተናግረዋል።   ዕውቅናው ከመሰጠቱ በፊት ሐረር ከተማን ከፕላስቲክ ቆሻሻ የፀዳች በማድረግ ያገለገሉ የፕላስቲክ ቁስን ዳግም ጥቅም ላይ ለማዋል አስቻይ ሁኔታ እንዳለ መገምገሙንም ጠቁመዋል። ኢኒሼቲቩ ለሴቶች እና ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩም በግምገማው መነሳቱን ነው አቶ ሔኖክ የተናገሩት። የሐረር ከተማን ከፕላስቲክ ቆሻሻ ነፃ ለማድረግ እና የፕላስቲክ ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም በዝቅተኛ ዋጋ የመኖሪያ ቤት ለመገንባት በኪዩቢክ ኢትዮጵያ እና ሐረር ከተማ መካከል በፈረንጆቹ ሚያዝያ 2024 ስምምነት መፈረሙን አውስተዋል።   የተጀመሩ ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ ዝናብ ያገኛሉ
Oct 22, 2025 187
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አስር ቀናት በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ቀደም ብሎ የክረምት ወቅት ዝናብ ሲያገኙ በነበሩት የምዕራብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ቀጣይነት ያለው ዝናብ ይኖራል። በሌላ በኩል በሰሜን ምዕራብ እና በሰሜን የሀገሪቱ ክፍሎች ወቅቱን ያልጠበቀ ቀላል መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች ያመላክታሉ ብሏል። የክረምት ወቅት ዝናብ እያገኙ የነበሩት የምዕራብና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚኖረው ርጥበት ለግብርና እንቅስቃሴ አዎንታዊ ሚና እንዳለው ገልጿል። በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት አካባቢዎች የሚጠበቀው ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ርጥበት በወቅቱ ለሚጀመር የግብርና ስራ ከፍተኛ ጠቃሜታ ይኖረዋል ብሏል። አብዛኛው የበጋ ርጥበት ተጠቃሚ ተፋሰሶች እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው የሚጠበቅ ሲሆን የተቀሩት ተፋሰሶች ዝቅተኛ ርጥበት እንደሚያገኙ የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች ያሳያሉ። ባሮ አኮቦ፣ ኦሞ፣ ጊቤ፣ መካከለኛውና ታችኛው ስምጥ ሸለቆ፣ ላይኛውና መካከለኛው ገናሌ ዳዋ፣ ላይኛውና መካከለኛ ዋቢ ሸበሌ፣ ታችኛው ኦጋዴን፣ ታችኛው ዓባይ እና ታችኛው ተከዜ መካከለኛ ርጥበት እንደሚያገኙ በመግለጫው ተጠቅሷል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው  
Oct 24, 2025 69
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡   በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡   ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡   በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀመረ
Oct 24, 2025 77
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦11ኛው የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተሞች በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው። በፎረሙ ላይ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች ምክክር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በቀጣናው መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከል የተጀመሩ የቅንጅት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኢጋድ
Oct 20, 2025 280
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። የኢጋድ ሶስተኛው የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት የሚኒስትሮች ስብሰባ ዛሬ በኬንያ ናይሮቢ ተጀምሯል። “በኢጋድ ቀጣና ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሰራተኛ ፍልሰት እና የሰዎች ዝውውር ህጋዊ ማዕቀፍን ማሻሻል” የስብሰባው መሪ ቃል ነው። በስብሰባው ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት የሰራተኛ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች፣ ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(አይኤልኦ)፣ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት(አይኦኤም)፣ የአውሮፓ ህብረትና የልማት አጋሮች ተገኝተዋል። በኢጋድ ቀጣና የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በቀይ ባህር መስመር ያለውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ከኢጋድ ቀጣና ውጪ የሚገኙ ዜጎች አባል ሀገራትን በነጠላ የመግቢያ ቪዛ መጎብኘት የሚያስችላቸውን የቪዛ ኢኒሼቲቭ ይፋ ይደረጋል። ኢኒሼቲቩ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርና ድንበር ተሻጋሪ ንግድን ማሳለጥ እንዲሁም ቱሪዝምን የማሳደግ ፋይዳ እንዳለው ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአውሮፓ ህብረት የፋይናንስ ድጋፍ የሚተገበረው ነጻ የሰዎችና የቁም እንስሳት እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፍ ሁለተኛ ምዕራፍ ይፋ ይሆናል። ማዕቀፉ ህጋዊ የፍልሰት መንገዶች ለማጠናከር እና ቀጣናዊ ትስስርን የማሳካት ግብ ያለው መሆኑንም አመልክቷል። ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ሰንሰለትን መበጣጠስ፣ በፍልሰት በሌላ ሀገር የሚገኙ ዜጎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ላይ ምክክር ያደርጋሉ። በውይይቱ ማብቂያ ሀገራት የጋራ መግለጫ እንደሚያወጡ የሚጠበቅ ሲሆን ደህንነቱ የተጠበቀ መደበኛ ፍልሰት፣ ጠንካራ የሰራተኛ አስተዳደር ስርዓት መፍጠርና ለሰዎች ዝውውር የተቀናጀ ቀጣናዊ ምላሽ መስጠት ላይ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እንደሚገልጹ ተጠቁሟል። ኢጋድ በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የጋራ ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመልክቷል። ዜጎች ህጋዊ አማራጮችን እንዲከተሉና የኢኮኖሚ ፈተናን ጨምሮ ለሌሎች ገፊ ምክንያቶች ዘላቂ መፍትሄ መስጠት በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ ገልጿል። ስብሰባው ጥቅምት 10 እና 11 በባለሙያዎች፣ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚኒስትሮች ደረጃ ይካሄዳል።
የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በቁርጠኝነት ሊተገብሩ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት
Oct 19, 2025 279
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) አፈጻጸም ውጤታማነት ለማሳደግ በትኩረት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብስባ ከጥቅምት 11 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች እና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገም እና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስ እና ዘላቂ የውሃና ተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩ ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚከናውን ኢዜአ ከህብረቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 529
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል።   ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው።   የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።   እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።   “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው።   ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል።   ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።   የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
 ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 560
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም።   በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል።   የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል።   በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል።   ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል።   በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።   በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 766
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።  
  "ያሆዴ"- ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት
Sep 28, 2025 846
(በማሙሽ ጋረደው - ከኢዜአ ሆሳዕና ቅርንጫፍ) የሀዲያ የአዲስ ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው። ለማህበራዊ የህይወት አመራር ጉልህ አስተዋጾም ስላለውም በሀዲያዎች ዘንድ በየዓመቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል፡፡ "ያሆዴ" ያለፈውን አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲስ ዘመን የሚቀበሉበት፤ የመጻኢ ተስፋ ብስራትና የልምላሜ ምልክትም ጭምር ተደርጎም ይቆጠራል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሲቀርብ የሀዲያ ተወላጆችና የበዓሉ ተሳታፊዎች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከያሉበት ወደአካባቢው በመምጣት ይሰባሰባሉ፡፡ በዘንድሮ የያሆዴ በዓልም የሀድያ ተወላጆች የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ በተዘጋጀ ስፍራ (ነፈራ) ተሰባስበው በዓሉን በድምቀት አክብረውታል፡፡ በበዓሉ አከባበር ያለፈው ዓመት ስኬትም ይገመገማል፤ በአዲሱ ዓመትም የተሻለ ተሰርቶ ስኬት እንዲመዘገብ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት ይካሄዳል። ሊተገበር የሚችል ዕቅድም ይታቀዳል፡፡ በግልና በቤተሰብ የመጡ ስኬቶች በጋራ በመሆን ይገመገማሉ። የበረቱና ውጤት ያስመዘገቡም እንዲበረታቱ ይደረጋል። ለዚህም ነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው የሚባለው። ሰዎች እንዲሰሩና ስኬት እንዲያስመዘግቡ የሚያበረታታ እሴት አለው። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፋን ቦጋለ እንደሚሉት የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል "ያሆዴ" ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት ነው፡፡ ከነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የበዓሉ መቃረብን የሚያበስሩት ታዳጊ ልጆች ናቸው። ልጆቹ የዋሽንት (ገምባቡያ) ድምጽ ማሰማት ከጀመሩ በጉጉት የሚጠበቀውን የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል መድረሱ ምልክት ነው። በዓሉ ሀድያዎች አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበት ወቅት ነው። በዓሉ የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት በመሆኑም የተለየ ትርጉምና ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች ተራርቀው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት ከያሉበት ይሰባሰባሉ። በዓሉ በአማረ መልኩ እንዲከበርም ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻቸውን ያከናውናሉ።   አባውራዎች ለበዓሉ ሠንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በቱታ ወይም በቅርጫ ቡድናቸው አማካኝነት እየቆጠቡ ይቆያሉ። እንዲሁም ለእንስሳት የሚሆን የግጦሽ ሳር የሚያበቅል ቦታ ከልለው ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሚሆነበት ምክንያት ደግሞ በዓሉ በሚከበርበት ሰሞን የሰው ልጅ ይቅርና እንስሳትም መጥገብ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ እማውራዎች ከበዓሉ ሦስትና አራት ወራት አስቀድመው እንሰት በመፋቅ ቆጮና ቡላ ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም ከአካባቢው እናቶች በጋራ በመሆን (ዊጆ) የተሰኘ የቅቤ እቁብ በመግባት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ማጠራቀም ይጀምራሉ፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ ለአተካናና ለሥጋ መብያ ናቀሮ ወይም ዳጣን እንዲሁም የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት ድርሻ የእናቶች ነው፡፡ ለበዓሉ የቤት ውስጥና የውጭ ግርግዳን በቀለምና በተለያዩ ጌጣጌጦች የማስዋብ ሃላፊነት ደግሞ የልጃገረዶች ነው። ወጣት ወንዶች ከነሀሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚያሳዩዋቸውን ግንድ በመቁረጥ ለምግብ ማብስያ እንዲውል ፈልጠው ያዘጋጃሉ። በሀዲያዎች አጠራር ለችቦ የሚሆን እንጨት ወይም ጦምቦራ ከጫካ ለቅመው አስረው እንዲደርቅም ያስቀምጣሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት የሚያደርገው ጥረት በዓሉ በስኬትና በድምቀት እንዲከበር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በዚህም ያሆዴ ከተናጠል ይልቅ ትብብርን የሚያጠናክር ነው ማለት ይቻላል። እሴቱ በትብብር መድመቅ እንደሚቻልም የሚያሳይ ነው።   ይህን ሀሳብ የሚጋሩት አቶ መስፍን የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል በምንም ሁኔታ መነጣጠል የማይቻል ትስስርን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ። ሀገራዊ አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር ዘመናትን የተሻገረና ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ባህላዊ እሴት ያለው መሆኑንም ይናገራሉ። በዓሉ ሊከበር ጥቂት ቀናት ሲቀረው አባውራዎች በቅርጫ ማህበራቸው አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ የእርድ በሬ ይገዛሉ። በዚህ ወቅት ገንዘብ ማዋጣት ያልቻሉ የቅርጫ አባላት እህል በሚደርስበት ወቅት ለመክፈል ተስማምተው በሬውን በዱቤ እንዲገዙ ይደረጋል፡፡ ይሄም የሚሆነው በያሆዴ በዓል አንዱ ሲበላ ሌላው ተመልካች መሆን ስለሌለበት ነው። እርስ በርስ መጨካከን እንዳይኖርና በዓሉን በአብሮነት ሁሉም ተደስቶ ማክበር እንዲችል ለማድረግ ነው። ከበዓሉ ዕለት በፊት ያለው የመጨረሻ ገበያም የእብድ ገበያ (መቻዕል ሜራ) የሚል ስያሜ አለው። ይሄ ሥያሜ ያገኘው በዓሉ ሲቃረብ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ውጥረት ታሳቢ በማድርግ ነው፡፡ በዚህ የእብድ ገበያ ህብረተሰቡ መገበያየት የሚጀምረው ጠዋት ማለዳ ጀምር ሲሆን የግብይት ሂደቱ የሚጠናቀቀው ደግሞ እኩለ ቀን ላይ ነው፡፡ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለመግዛትና የያሆዴ በዓል ከተከበረ በኋላ ለአንድ ወር ገበያ ስለማይቆም ይህን ታሳቢ ያደረገ ግብይት ለመፈጸም የግብይት ሂደቱ ጥድፊያ የበዛበት ሆኖ ይታያል።   ያሆዴ በዓል መከበር የሚጀምረው በአተካን ሂሞ ወይም በአተካና ምሽት ሲሆን ይህም ከበዓሉ አንድ ቀን በፊት ያለው ምሽት ነው። ስያሜውን ያገኘው "አተካና" ከተሰኘና በያሆዴዎች ዘንድ ለክብር እንግዳ እና በዘመን መለወጫ ከሚዘጋጅ ምግብ ነው። አተካና ከወተት፣ ከአይብ፣ ከቡላ፣ ከቅቤና ከሌሎች የቅመማ ቅመም ውጤቶች የሚዘጋጅ ምግብ ሲሆን በጣም ጣፋጭና የምግበ ፍላጎትን የሚጨምር ምግብ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ይሄንን የተለየ ምግብ ተሰባስቦ በአብሮነት በመመገብ በደመቀ መልኩ በዓሉን ማክበር ይጀምራል፡፡ የአካባቢው አባቶች በወጣቶች የተዘጋጀ የማቀጣጠያ እንጨት (ሳቴ) ይዘው ትልቅ በሚባሉ አባውራ ቤት ደጃፍ ወደ ተዘጋጀው የችቦ ደመራ (ጦምቦራ) ቦታ ይመጣሉ:: የሀገር ሽማግሌች አዲሱ ዓመት የብርሃን ዓመት እንዲሆን፤ ለሀገርና ለህዝቦቿ ሰላም እንዲጸና፤ አብሮነት እንዲጠናከር፣ ሰላምና ፍቅር እንዲነግስ ፈጣሪያቸውን ከተማጸኑ በኋላ ችቦውን በእሳት ይለኩሳሉ፡፡   ችቦው ከተለኮሰ በኋላ የአካባቢው ወጣቶች ተሰባስበው ያሆዴ …ያሆዴ! …ያሆዴ! በማለት እየጨፈሩ ያነጋሉ ይጨፍራሉ:: በሀድያዎች ዘንድ "ያሆ" ማለት የአዲስ ዓመት መግባትን ተከትሎ ማብሰሪያ ጭፈራ ሲሆን "ኤዴ" ማለት ደግሞ አገናኝ ማለት ነው፡፡ በያሆዴ በዓል የእርድ ሥነ ስርዓት ለማከናወን ነዋሪዎች የሚሰበሰቡበት ስፍራ "ነፈራ" የሚል ስያሜ አለው። የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሰፋ ያለ ቦታ ሰሆን በተለያዩ የጥላ ዛፎች የተዋበና ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀም ነው። በእለቱ ለእርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኋላ የባህል ሽማግሌዎች የበሬውን ሻኛ በሰርዶ ሳር ለጋ ቅቤ ይቀባሉ፤ ወተትም ያፋሱበታል፡፡ ይህ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ጋቢማ የሚባል ሲሆን (የመልካም ምኞት) መግለጫ ስነ ስርዓትም ነው፡፡ ይህም ሥነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም "ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሀገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን " እያሉ በአባቶች ምርቃት ከተካሄደ በኋላ የእርድ ስነ ስርዓት ይከናወናል፡፡ የእርድ ሥነ ስርዓቱ የተከናወነበት ቤት እማወራ አስቀድመው ባደረጉት ዝግጅት መሰረት ቅቤ፤ (ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ) እንዲሁም ከታረደው የበሬ ሥጋ አርዚ ማራ (ቅምሻ) ይወሰድና ክትፎ ከተዘጋጀ በኋላ በጋራ እየበሉ እየተጫወቱ ይውላሉ፡፡ በዚህም በቅርጫ ሥጋው ላይ ከሚሳተፉት የቤተሰብ አባላት ውጪ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችም ጭምር አብረው በመብላት በመጠጣት በዓሉን በአንድነት ያሳልፋሉ፡፡ ቀሪውን የቅርጫ ሥጋም አባላቱ ተከፋፍለው ወደ እየቤታቸው ይወስዱታል፡፡ በዓሉ አብሮ የመብላት፣ የመጠጣት፣ የመጠያየቅ፣ ችግርንና ግጭትን በጋራ ተወያይቶ የመፍታት፣ መፈቃቀርና መተሳሰብን የሚፈጥር፣ አቅመ ደካሞችና የተቸገሩ የሚረዱበት የአብሮነት መገለጫ በመሆኑ በተለየ መልኩ ይከበራል፡ ከእርድ ሥርዓቱ በኋላ በማግስቱ ልጆች አደይ አበባ (ዘራሮ) ይዘው ወደ ወላጆቻቸው እየጨፈሩ ይመጣሉ። የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባላሉ። ከስጋውም፣ ከቦርዴውም፣ ከአተካናውም እንዲመገቡ ያደረጋል። ይህ ስነ ስርዓትም ሚክራ ይባላል። በያሆዴ የዘመን መለወጫ በዓል ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ሥጋና አደይ አበባ ጭምር ይዘው ይሄዳሉ። በዓሉ ያላገቡ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ለአዲስ ህይወት ጅማሬ የሚያበስሩበት በመሆኑን የተለየ ድባብ አለው፡፡ የያሆዴ በዓል ካሉት እሴቶች አንዱ የህብረተሰቡን የአካባቢ ልማት ተሳትፎ ማበረታታት ተጠቃሽ መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ዕሴቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናቅቀው ለማህበረሰብ ጥቅም እንዲውሉ ጭምር አቅም እየሆነ መምጣቱን ነው የሚናገሩት።ይህ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የማህበራዊ መስተጋብር መጋመጃ የሆነው በዓል እሴቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል መስራት ይገባል። እሳቸው እንዳሉት በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማስቻል እየተሰራ ነው፡፡ ለዚህም መምሪያው ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ዕሴቱን የመሰነድና ምርምሮች ማካሄድን ጨምሮ እያከናወናቸው ያሉ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።  
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1277
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1880
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2701
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2841
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 582
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 458
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6305
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4785
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 55123
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51057
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 31784
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 29292
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 25859
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 24408
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24163
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 24004
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 55123
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51057
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 31784
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 29292
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የአፍሪካ የግብርና፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ፤ እድሎች እና ፈተናዎች
Oct 20, 2025 341
አፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማሳካትና እንድትበለጽግ የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ መዕራፍ ላይ ይገኛል። የአህጉሪቱን የመለወጥ ትልም ባሏት እምቅ ተፈጥሯዊ ጸጋዎች ላይ የተመረኮዘ ነው። ተዝቆ የማያልቀው የአፍሪካ ብዝሃ ሀብት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግና አይበገሬ አቅም መገባንት የሚያስችሏትም ጭምር ናቸው። ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ ሀብቶቿ እና ብዝሃ ከባቢ የአየር ንብረቷ ከሀብቶቿ መካከል ይጠቀሳሉ። ግብርና አሁንም የአፍሪካ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው። ዘርፉ ለአህጉሪቱ 35 በመቶ የሚጠጋ አጠቃላይ ጥቅል ሀገራዊ ምርት(ጂዲፒ) አስተዋጽኦ ያደርጋል። 60 በመቶ ህዝብም በግብርና ስራ እንደሚተዳደር የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) ሰነድ ያሳያል። ከዚህም ውስጥ አብዛኞቹ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው።   ሴቶች በግብርናው ዘርፍ ካለው የሰው ኃይል የ50 በመቶ ድርሻው ይወስዳሉ። የአፍሪካ ህዝብ 60 በመቶ ድርሻ የያዘው ወጣት በግብርና ንግድ፣ እሴት መጨመርና የኢኖቬሽን ስራዎች ያለው ተሳትፎ እያደገ መጥቷል። የዓለም 60 በመቶ ያልለማ መሬት ያለው በአፍሪካ ነው። ሰፊ የውሃ ሀብቶችና እያደገ ያመጣው ብሉ ኢኮኖሚ(የባህር እና ሌሎች የውሃ ሀብቶች) ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ እድገትን የሚያረጋግጡ ናቸው። የመሰረተ ልማቶች ተደራሽነት ማደግ፣ ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶችና ኢኖቬሽንን የተመረኮዙ የፋይናንስ አማራጮችን መስፋት ግብርናን የምግብ ምንጭ ብቻ ሳይሆን ለኢንዱስትሪ ልማት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ እና ንግድ መሳለጥ ትልቅ አቅም መሆን ይችላል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በግብርና ምርቶችና አገልግሎቶች ያለውን አህጉራዊ የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ በማሳደግ ረገድ ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ ነው። የንግድ ቀጣናውን በሚገባ መጠቀም ከተቻለ እ.አ.አ በ2030 የግብርና ንግድ ልውውጡን በ30 በመቶ ማሳደግ እንደሚቻል ጥናቶች ያመለክታሉ። ግብርናው የተጠቀሱት ጥንካሬዎች ያሉት ቢሆንም ረጅም ጊዜ የዘለቁ መዋቅራዊ ፈተናዎች አብረውት ዘልቀዋል። የግብርና ምርቶች ላይ የሚፈለገውን ያህል እሴት አለመጨመር፣ የቴክኖሎጂ አጠቀቃምና የምርታማነት ውስንነት፣ የመሰረተ ልማቶች እና ሎጅስቲክስ በበቂ ሁኔታ አለመሟላት፣ ተቋማዊና አስተዳደራዊ ክፍተቶች ከአየር ንብረት ለውጥና ሌሎች ተፈጥሯዊ አደጋዎች እንዲሁም እያደገ ከመጣው ህዝብ ጋር ተዳምሮ ግብርናውን እየፈተነው ይገኛል።   ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ማጠንጠኛ የሆነው ጉዳይ የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት(ካዳፕ) ነው። እ.አ.አ በ2003 የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ ባደረገው ስብሰባ የግብርና የምግብ ዋስትና ድንጋጌን አጽድቋል። ይህ ማዕቀፍ የማፑቶ ድንጋጌ ስያሜን በማግኘት የካዳፕ ትግበራ በይፋ እንዲጀመር አድርጓል። የማፑቶ ድንጋጌ እ.አ.አ በ2014 በማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025 የተተገበረ) በአዲስ መልክ የታደሰ ሲሆን የተለያዩ ቃል ኪዳኖችን በውስጡ ይዟል። ይህም በካዳፕ አማካኝነት የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ከአጠቃላይ ዓመታዊ ጥቅል ምርታቸው(ጂዲፒ) ቢያንስ ስድስት በመቶውን ለግብርናው ዘርፍ እንደሚመድቡና በየሀገራቱ በዘርፉ በየዓመቱ በአማካይ ስድስት በመቶ እድገትን የማሳካት ግብ አለው። ረሃብን ማጥፋት፣ ድህነትን በግማሽ መቀነስ፣ የማይበገር አቅም መገንባትና የጋራ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ሌሎች ግቦች ናቸው። ካዳፕ የአፍሪካ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ያላቸውን ኢንቨስተመንት በማሳደግ፣ በአፍሪካ የእርስ በእርስ የግብርና ንግድን በማሳደግና የፖሊሲ መሰናሰልን በመፍጠር ቁልፍ ሚና ተወጥቷል። ይሁንና የተመዘገቡት ውጤቶች ያልተመጣጠነ ልዩነት የሚታይባቸው ናቸው። የ2023 የካዳፕ የግምገማ ሪፖርት እንደሚያሳየው የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የማላቦ ግቦችን ማሳደግ የሚያስችል መንገድ ላይ እንዳልሆኑ ያስቀምጣል። ይሁንና 26 ሀገራት በተቀመጡ ግቦች መመዘኛ መሻሻል እንዳሳዩ ይገልጻል። ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ካሜሮን፣ ግብጽ፣ ማሊ፣ ጋና እና ጋምቢያ የተሻለ አፈጻጸም ካላቸው ሀገራት መካከል ይጠቀሳሉ። አብዛኞቹ ሀገራት በግብርና ኢንቨስትመንት፣ ምርታማነት እና የፖሊሲ ትግበራ ላይ ፈተናዎች እንዳሉበት ሪፖርቱ አመልክቷል። ሀገራት የሰነዱን ትግበራ ማፋጠንና ተቋማዊ ቅንጅትን ማጠናከር እንደሚገባቸው አሳስቧል።   የማላቦ ድንጋጌ ወደ መገባደዱ ላይ የሚገኝ ሲሆን የካዳፕ ቀጣዩ ምዕራፍ የካምፓላ ድንጋጌ ነው። ይህ የትግበራ ምዕራፍ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚቆይ ነው። የካምፓላ ድንጋጌ ከማፑቶ እና ማላቦ ድንጋጌዎች ትምህርቶችን በመውሰድ የግብናውን እድገት ማላቅ ግቡ አድርጎ ይዟል። የካምፓላ አጀንዳ ኢኖቬሽን፣ ዲጂታላይዜሽን፣ አረንጓዴ እድገት እና አይበገሬነት ያላቸውን ሚና በማንሳት መስኮቹ ስርዓተ ምግብን ዘላቂና አካታች የማድረግ ግብን ማሳካት እንደሚያስችሉ አመልክቷል። በዚህ ማዕቀፍ እ.አ.አ 2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ህዝብ ይኖራታል ተብሎ የሚጠበቀውን አፍሪካን በራስ አቅም የመመገብ ውጥን የያዘ ነው። ይሁንና የግብርና ምርታማነት ከዓለም አቀፍ አማካይ የምርታማነት ምጣኔ አንጻር ሲታይ አሁንም ወደ ኋላ ቀረት ያለ ነው። ይህም አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች የተገደበ የፋይናንስ አቅርቦት ማግኘታቸው እንዲሁም የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትና የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው አለመደረጉ የችግሩ አብይ መንስኤ ሆኖ ይጠቀሳል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎችና የከባቢ አየር ብክለት ፈተናዎቹ እንዲበረቱ አድርጓል። ዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ የበይነ መንግስታት ፓናል(IPCC) አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እርምጃዎችን በፍጥነት ካልወሰደች እ.አ.አ በ2050 የግብርና ምርታማነቷ ከ20 እስከ 30 በመቶ ሊቀንስ እንደሚችል ገምቷል። ከ250 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ አፍሪካውያን ደህንነቱ ያልተረጋገጠ እና ንጽህናው ያልተጠበቀ የውሃ አቅርቦት ፈተና ውስጥ ይገኛሉ። በህዝብ ቁጥር መጨመር፣ በከተሜነትና ኢንዱስትሪ መስፋፋት ምክንያት ንጹህ የውሃ አቅርቦትን የማግኘት ጉዳይ የበለጠ ሊስፋ እንደሚችል ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩና ፈተናዎች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ለአባል ሀገራት የፋይናንስ እና የቴክኒክ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል። የህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር የስራ ክፍሉ(DARBE) አማካኝነት የአፍሪካን ፖሊሲዎች፣ ፕሮግራሞችና ኢኒሼቲቮች የተናበቡና የጋራ ግብ ያላቸው እንዲሆኑ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል። የአቅም ግንባታ፣ የቴክኒክ እና የፖሊሲ ድጋፍም የሚያደርግ ሲሆን ብሄራዊ እቅዶች ከአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሰነዶችና የአጋርነት ማዕቀፎች ጋር የተጣጠሙ መሆናቸውን ያረጋገጣል። የስራ ክፍሉ ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች ጋር አጋርነቶችን የማጠናከር ስራ ያከናውናል። ግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት እንዲሁም የተፈጥሮ እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በዘላቂነት መጠቀም ላይ የተቀናጁ አሰራሮችን መፍጠር ላይም ይሰራል። የዘርፉ አጠቃላይ ስራዎች አካል የሆነው ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎችና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገምና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም(ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ(ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስና ዘላቂ የውሃና የተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩም ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚያከናውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። አፍሪካ ወደ ዘላቂ ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር እና አካባቢ ጥበቃ እያደረገች ያለው ጉዞ አንገብጋቢ አጀንዳና ሽግግሩን ለማፋጠን ወሳኝ ሚና አለው። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የፋይናንስ ማነቆ፣ መሰረተ ልማቶች እና የፖሊሲ የመፈጸም አቅም ውስንነትን ጨምሮ የተለያዩ ፈተናዎች ቢኖሩባትም እድሎቿ ፈርጀ ብዙ ናቸው። በርካታ ያልለማ መሬት፣ ሰፊ የውሃ ሀብት፣ ወጣቶች እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በአፍሪካ ዘላቂ የግብርና እድገት ለማረጋገጥና ሁሉን አቀፍ ስርዓተ ምግብ ለመገንባት የሚያስችል ነው። ለአርሶ አደሮች በቂ የፋይናንስ አቅርቦት ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ አቅማቸውን መገንባት ቁልፍ ጉዳይ ነው። ሀገራት ብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸውን ከአህጉራዊ ማዕቀፎች ጋር ማጣጣም ይኖርባቸዋል። ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋት ይገባል። የተፈጥሮ ሀብትን በሚገባ መጠቀም፣ በኢኖቬሽን ላይ መዋዕለ ንዋይን ፈሰስ ማድረግና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች፣ አረንጓዴ እና የበለጸገች አህጉር መገንባት ይቻላል።
ኢሬቻ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ማንሰራራት!
Oct 3, 2025 966
ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ሰዎች በክረምት ወቅት ከሚከሰት መለያየትና መራራቅ በኋላ ዳግም የሚገናኙበት፣ በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት ዕለት ነው። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። ኢሬቻ የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ጥብቅ ቁርኝት የሚገለጽበት የገዳ ስርዓት አንዱ አካል ነው፡፡ የኢሬቻ እሴቶች ጠንካራ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ያላት ሀገር ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው። አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ አብሮነት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ዕርቅ እና ሌሎችም ተጠቃሽ የመልካም እሴቶች መገለጫ ነው። በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አንዱ እሴት ኢሬቻ ሲሆን፤ ለሀገር ማንሠራራትና ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሠረት ይሆናል፡፡ ኢሬቻ አብሮነት የሚጸናበት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ይበልጥ የሚጎላበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጎለብትበት፣ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ማሰሪያ ከፍ ያለ በዓል ነው፡፡ ኢሬቻ በጋራ የሚያከብሩትና የዓለም ቱሪስቶች የሚታደሙበት ሲሆን፤ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል አከባበር ሀገራዊ ማንሰራራት በተግባር የተረጋገጠበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ዓለም የኢትዮጵያን መቻል በተግባር ባየበትና ሌሎች ለሀገር ማንሰራራት ዕውን መሆን መሠረት የሚጥሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኘሮጀክቶች ይፋ በተደረጉበት ማግስት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡   በዓሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመላው ኢትዮጵያዊያንን ሕብረት የሚንጸባረቅበት ሆኖ በተለያዩ አከባቢዎች በድምቀት እየተከበረም ይገኛል፡፡ በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Waaqa Uumaa, Waaqa Uumamaa ፍጥረትን የፈጠርክ ፈጣሪ Gurraacha garaa garbaa የእውነትና የሰላም አምላክ! Dogoggora nu oolchi ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! Dacheef nagaa kenni ለምድራችን ሰላም ስጥ! Laggeenif nagaa kenni ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! Olota keenyaaf nagaa kenni ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! . . . Loowan keenyaaf nagaa kenni " ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "አሜን! አሜን! አሜን!” ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 25 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ " ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት " በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" Irreecha Birraa (በውኃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን፤ በዓመቱ አጋማሽ ላይ "ኢሬቻ ቱሉ" Irreecha Arfaasaa ደግሞ በተራራማ ቦታ ይከበራል። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ነው። የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመምጣቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ይህ ከማህበራዊ መስተጋብር አኳያም ሰዎች የሚሰባሰቡበትና የሚገናኙበት ነው። ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ብርሃን (ብራ) ስለደረሰ ለዚያ ምልክት ይሆን ዘንድ የለመለመ እርጥብ ሣር ይዘው ወደ ወንዝ በመውረድ ንጹህ ውሃ ውስጥ እየነከሩና እየረጩ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ አብሮነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። ኢሬቻ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው "ዋቃ" "Waaqa" ምስጋናውን ለማድረስ የሚከበር ሲሆን፤ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲከበር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። ኢሬቻ የወንድማማችነትና የአንድነት አርማ ሲሆን፤ የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ፣ የህብረ ብሔራዊ አብሮነት ማስተሳሰሪያም ጭምር ነው፡፡ በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይበዛል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል፣ አንድነት ይጸናል። ኢሬቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ነው። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ስለሆነም ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር እንዲህ እያሉ ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። የበዓሉ ታዳሚዎች ከዋዜማው ጀምሮ በሆረ ፊንፊኔና በሆረ ሀርሰዲ በመሰባሰብ፤ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎችን በማዜምና ምስጋና በማቅረብ አድረው በነጋታው ዋናውን የምስጋና በዓልም ያከናውናሉ፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የደስታና የምስጋና ምልክት የሆነውን ባህላዊ ነጫጭ ልብስ ለብሰው፣ ባህልን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ሁነቶችን በመከወን ልዩ ልዩ ዜማዎችን በማዜም፣ ግጥሞችን በማቅረብ፣ ወደ ፈጣሪ በመጸለይ እና ምስጋና በማቅረብ ሥርዓቱን ያከናውናሉ፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ከማቀራረብና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጾኦ ያለው ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገር የመጡ ልዑካን በበዓሉ ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። የኢሬቻ በዓል ለቱሪዝም ፍሰት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ጉልህ ነው፤ በርካታ የባህር ማዶ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የሚታደሙበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ ሲሆን፤ ዘርፉን በማጠናከር እና ብሔራዊ ልማትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚናንም የሚጫወት ነው፡፡ ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!        
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም