ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ተቋርጦ የነበረው የቴሌቪዥን ስርጭት ተመለሰ
Nov 14, 2025 32
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ተቋርጦ የነበረው የቴሌቪዥን ስርጭት ተመልሷል። የሳተላይት አቅራቢ ድርጅት በሆነው SES የቴሌ ፖርት ላይ እስራኤል አካባቢ ባጋጠመው ከፍተኛ የአየር ፀባይ ለውጥ ምክንያት የኃይል መቋረጥ ተፈጥሮ ነበር፡፡ በዚሁ ምክንያት ኢቢሲ ፤የፋና ቴሌቪዥን እና የአብዛኛዎቹ የሀገራችን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ስርጭት ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፤ አገልግሎቱን ለመመለስ በተሰራው ሥራ የቴሌቪዥን ስርጭቱ ተመልሷል።
በሳተላይት ችግር ምክንያት የቴሌቪዥን ስርጭት መቋረጥ አጋጥሟል
Nov 14, 2025 43
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 5/2018(ኢዜአ)፦የሳተላይት አቅራቢ ድርጅት በሆነው SES የቴሌ ፖርት ላይ እስራኤል አካባቢ ባጋጠመው ከፍተኛ የአየር ፀባይ ለውጥ ምክንያት የኃይል መቋረጥ መፈጠሩን ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ገለጸ፡፡ በዚሁ ምክንያት የፋና ቴሌቪዥን እና የፋና ፕላስ እንዲሁም የአብዛኛዎቹ የሀገራችን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ስርጭት ተቋርጧል፡፡ አገልግሎቱን ለመመለስ እየተሰራ በመሆኑ በትዕግስት እንዲጠብቁም ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን አስታውቋል።
ለብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከባበር በመሰረተ ልማት አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ነው - የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር
Nov 14, 2025 48
ሆሳዕና፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሆሳዕና ከተማ ለሚከበረው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በመሰረተ ልማት አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። 20ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለሀብረብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ይከበራል። በዓሉ በፌደራል ደረጃ በሚከበርበት ሆሳዕና ከተማ ከማክበሪያ ስፍራና እንግዶች ማረፊያ ጀምሮ የተለያዩ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው። በዝግጅት ምዕራፍ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች በዋናነት ይጠቀሳሉ። የሆሳዕና ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ዕህፈት ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ተከተል ጩፋሞ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በከተማው በፌዴራልና በከተማ አስተዳደሩ ከ30 ኪሎ ሜትር በላይ የአስፓልት መንገድ ሥራ እየተከናወነ ነው፡፡ በከተማ አስተዳደሩ በመጀመሪያ ምዕራፍ የ12 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነና ልማቱ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ከተማዋን ተወዳዳሪና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚገነቡ የመሰረተ ልማት ሥራዎች የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀን በዓልን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይ የመንገድ መሰረተ ልማቱን ከበዓሉ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ትኩረት መሰጠቱን ነው ያመለከቱት። በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሶዶና አካባቢው ፕሮጀክቶች ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ሰለሞን ሞላ በበኩላቸው እንዳሉት ተቋሙ በራሱ ወጪ በከተማው የ10 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ያከናውናል። የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ አካል የሆነው የ4 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራን በተያዘው ወር መጨረሻ በማጠናቀቅ ለበዓሉ ለማድረስ ርብርብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የኮሪደር ልማቱ ሥራው የተሽከርካሪና የእግረኛ መንገዶችን ጨምሮ የመዝናኛ፣ የአረንጓዴ ስፍራዎች፣ የመንገድ አካፋይና መብራቶችን ባካተተ መልኩ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የመሳይ ኦሊ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ የሆሳዕና ከተማ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ታደሰ አማኑኤል በበኩላቸው፣ ልማቱን በታቀደው ጊዜ ለማጠናቀቅ ቀንና ማታ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የኮሪደር ልማት ሥራውን ለኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ለማድረስ በርብርብ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል። በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ከተማዋን ለነዋሪው ምቹ ከማድረግ ባለፈ ከአቻ ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ የሚያደርጋት ነው ያሉት ደግሞ የከተማው ነዋሪ እሸቱ ኃይሌ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በከተማው መከበር የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተናግረዋል፡፡
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና ሁለተኛ ድሉን አሳክቷል
Nov 14, 2025 36
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የስድስተኛ ሳምንት ጨዋታ ሲዳማ ቡና አዲስ አበባ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ምትኬ ብርሃኑ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥራለች። የግቦቹ ባለቤት የሆነችው ምትኬ ብርሃኑ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። ውጤቱን ተከትሎ ሲዳማ ቡና በዘጠኝ ነጥብ ደረጃውን ከስድስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አዲስ አበባ ከተማ በሶስት ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቀን ላይ በተደረገ ጨዋታ የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሃዋሳ ከተማን 3 ለ 2 አሸንፏል።
ኢንተርፕርነርሽፕ ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ አቅም ጥቅም ላይ እንድታውል እያደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
Nov 14, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ ኢንተርፕርነርሽፕ ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ አቅም ጥቅም ላይ እንድታውል እያደረገ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ከህዳር 8 እስከ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደውን ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም መንግስት የኢንተርፕርነርሽፕ ሥራን ለማስፋት ቁርጠኛ በመሆኑ ዘርፉ ትልቅ ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አመራር የማይበገር ሀገር ለመገንባት ለዘርፉ ትኩረት በመስጠቱ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። ኢንተርፕርነርሽፕ ከሥራ ፈጠራና የሰው ሀይል ልማት ባለፈ ሀገር የመገንባት ጉዳይ መሆኑንም አንስተዋል። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ ተቋማት እሴት መፍጠር እንዳለባቸው ያምናል ያሉት ሚኒስትሯ፤ በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተመዘገበው ለውጥ ማሳያ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የኢንተርፕርነርሽፕ ዘርፉን ማገዝ እንደሚገባ በመጠቆም፤ የዘንድሮው የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት እንደሀገር ከያዝነው እሳቤ ጋር ይጣጣማል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ጉዞ ተጀምሯል ያሉት ሚኒስትሯ፣ በእስከ አሁን የተመዘገቡና የታዩ ለውጦች እንደምንችል ማሳያ ናቸው ነው ያሉት። ጉዟችን የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና እስከሚረጋገጥ በመሆኑ ረጅሙን ጉዞ በፈጠራና ኢንተርፕርነርሽፕ ማገዝ ይገባል ብለዋል። ዓለም አቀፉ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ከህዳር 8 ቀን ጀምሮ ለአስር ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ሁነቶች እንደሚካሄድም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በኢንተርፕርነርሽፕ ግዙፍ መሆኗን በማንሳት ይህም በዘርፉ በዓለም ሥነ ምህዳር ኢትዮጵያ የሚታይ ስራ እንዳላት ያመለክታል ብለዋል። መርሀ ግብሩ በዘርፋ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው መስራት የሚፈልጉ ተቋማትን የምናገኝበት ይሆናል ያሉ ሲሆን የስታርታፕ አዋጁን ጨምሮ የተወሰዱ እርምጃዎች መንግስት ለዘርፉ እድገት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ያመላክታል ነው ያሉት።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ከጎረቤቶቿ ጋር አብሮ የማደግ ፍላጎቷን ለማሳካት እየሰራች ነው - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)
Nov 14, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ከጎረቤት ሀገሮች ጋር አብሮ የማደግና የመበልጸግ ፍላጎቷን ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) አስታወቁ። "ሆርን ሪቪው" የተባለው ቲንክ ታንክ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ትናንት የፖሊሲ ፎረም አካሂዷል። በፎረሙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡና አጋር አካላትን ጨምሮ ፖሊሲ አውጪዎችና ምሁራን የታደሙ ሲሆን፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ(ዶ/ር) በአፍሪካ ቀንድ በተለይም በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም፤ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ግጭትና አለመረጋጋት ዋነኛ መገለጫ እየሆነ መጥቷል በሚል ከሁሉም የሚዲያ አማራጮች መስማት የተለመደ ነው። ቀጣናው ሰፊ የሚታረስ መሬት፣ የውሃ ሀብት፣ እምቅ የተፈጥሮ ማዕድንና ጠንካራ ሰራተኛ ሕዝብ ያለው መሆኑን አመልክተው፤ በአካባቢው በሚፈጠሩ ግጭቶች ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ አዳጋች እንዳደረገውም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ይህን ለረጅም ጊዜ የልማት፣ የሰላምና የደህንነት ስጋት የሆነውን ቀጣና ለመቀየር በመሰረተ ልማትና በኢኮኖሚ ትስስር እንዲፈጠር ጥረቶች እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ቅድሚያ ለጎረቤት የሚሰጥ፣ ከሁሉም ጋር በሰላማዊና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ አብሮ የመስራት ዓላማ መያዙን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገሮች ጋር በሰላማዊና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ አብሮ የማደግ ፍላጎቷን በመሰረተ ልማትና በኤሌክትሪክ ሃይል ትስስር በተግባር ማሳየቷንም አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት እያደገ ከመጣው የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር አኳያ እንዲሁም እየተመዘገበ ያለውን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስቀጠል የባህር በር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ ቀደም ባሉት ዓመታት የባህር በር የነበራት ሀገር ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንድታጣ መደረጉን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ እና ኤርትራ አንድ ሀገር እንደነበሩ ያስታወሱት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ በወቅቱ ኢትዮጵያን የመሩ መንግስታት ሃላፊነት በጎደለው መልኩ ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠልና ከባህር እንድትነጠል ማድረጋቸውን አመልክተዋል። በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ለዘመናት የዘለቀው ግጭት መነሻ ከድንበር ውዝግብና ከባህር በር ፍላጎት የተሻገረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የኢትዮጵያን የሰላምና የልማት ፍላጎት በየጊዜው የሚገዳደር መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኑን ያብራሩት ሚኒስትሩ፤ ሁሉም ሀገሮች ለዚህ ሊተባበሩ ይገባል ብለዋል። የውጭ ጣልቃ ገብነትን መከላከልና የንግድና ኢንቨሰትመንት ግንኙነትን ማሳደግ ለቀጣናዊ ኢኮኖሚ ውህደት መሳካት ወሳኝ መሆኑንም ነው ያነሱት። እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፤ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም ዘላቂ ልማትን ለማምጣት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፉን ማጠናከር አለበት። ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ከሰሩ ለሌሎች ሀገሮች ምሳሌ የሚሆን ትብብር መፍጠር እንደሚችሉም ተናግረዋል።
በሶማሌ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል
Nov 14, 2025 49
ጅግጅጋ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር ተገለጸ። በክልሉ አከባበሩን በተመለከተ የዝግጅቱ አብይ ኮሚቴ በአከባበሩ ዙሪያ ዛሬ ተወያይቷል። የሶማሌ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ መሀመድ አዳን እንደገለጹት በክልሉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል። በክልሉ በዓሉ በወረዳ፣ በዞንና በከተማ አስተዳደሮች ከዛሬ ጀምሮ እስከ ህዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም በደም ልገሳ፣ በንግድና ባዛር፣ በችግኝ ተከላ፣ በስፖርታዊ ውድድሮች፣ በፓናል ውይይት፣ አረጋውያንን በመደገፍና በሌሎች ዝግጅቶች እንደሚከበር ተናግረዋል። በክልል ደረጃ ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም በጅግጅጋ ከተማ የበዓሉ ማጠቃላይ ፕሮግራም እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለጋራ ልማትና ዕድገት በአንድነት እንድንተጋ መነሳሳትን ፈጥሯል - የመንግስት ሰራተኞች
Nov 14, 2025 53
ወልዲያ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለጋራ ልማትና ዕድገት ሁላችንም በህብረ ብሔራዊ አንድነት እንድንተጋ መነሳሳት ፈጥሮልናል ሲሉ የወልዲያ ከተማና የሰሜን ወሎ ዞን የመንግስት ሠራተኞች ተናገሩ። በአገራችን የሚከበረው 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ብሄራዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በወልዲያ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። ውይይቱ ላይ የተሳተፉ የመንግስት ሠራተኞች እንዳሉት፤ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለጋራ ልማትና ዕድገት በህብረ ብሔራዊ አንድነት እንድንተጋ መነሳሳትን ፈጥሯል። ከተሳተፊዎቹ መካከል አቶ ታምራት ወራሴ በዓሉ ስለ ህገ መንግስት፣ ዴሞክራሲና የፌደራል ስርዓት ፋይዳ ዙሪያ እውቀት እንድንጨብጥ አስችሎናል ብለዋል። የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች አገር የሆነችው ኢትዮጵያ የህዝቦቿ አንድነት ዛሬም በእኛ ዘመን ተጠናክሮ እንዲቀጥል የጋራ ትርክት ላይ በማተኮር መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል። ነጠላ ትርክትን በማስወገድ ለጋራ ልማትና ዕድገት በአንድነት ልንተጋ ይገባል ያሉት ደግሞ ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ጀማል ሙሐመድ ናቸው። የህገ-መንግስቱ መልካም ትሩፋቶች ለጋራ ተጠቃሚነታችን ፈር ቀዳጅ በመሆናቸው ተጠብቆ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ማዋል ይገባል ብለዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊና ውይይቱን የመሩት አቶ ፍስሃ መንግስቴ በበኩላቸው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀንን ስናከብር ለህዝቦች ሠላም፣ ፍቅርና አንድነት በመስራት መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። በዓሉን ስናከብር በህብረ ብሔራዊ አንድነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ሃገረ መንግስትን እውን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሊሆን ይገባልም ብለዋል። የዘንድሮውን በዓል ለየት የሚያደርገው የህዳሴ ግድባችን ባስመረቅንበት ማግስት የሚከበር በመሆኑ ደስታችንን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል ያሉት ደግሞ የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ አቶ ኢትዮጲስ አያሌው ናቸው። በዓሉን ስናከብርም በህብረ ብሔራዊ አንድነት የተገነባችውን ኢትዮጵያ ወደፊት ለማሻገር ቁርጠኛነታችንን በማረጋገጥ መሆን አለበት ብለዋል። በመድረኩ ላይም የወልዲያ ከተማ አስተዳደር፣ የሰሜን ወሎ ዞን የመንግስት ሠራተኞችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት "ዴሞክራሲና የኢትዮጵያ ፌደራል ስርዓት" በሚል ርእስ ውይይት አካሄደዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እንግዶቹን መቀበል የሚያስችል የተሟላ ዝግጅት አድርጓል - ምክር ቤቱ
Nov 14, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ለማክበር የሚመጡ እንግዶቹን ለመቀበል የተሟላ ዝግጅት ማድረጉን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ገለጹ። ምክትል አፈ ጉባኤዋ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአጭር ጊዜ በዓሉን ለማስተናገድ ያከናወነው ቅድመ ዝግጅት የሚደነቅ ነው። እንደ ክልል አብዛኛዎቹ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን አንስተው፤ ቀሪ ስራዎችን በቀሩት ጊዜያት እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል። በዓሉን የክልሉን ሁለንተናዊ አቅሞች ለማስተዋወቅ መጠቀም ይገባል ሲሉም ምክትል አፈ ጉባኤዋ አሳስበዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤት ሀላፊ ትግሉ መለሰ በበኩላቸው፤ ክልሉ በአጭር ጊዜ የመሰረተ ልማት ክፍተቶችን ለማሟላት ያደረገው ዝግጅት ሰፊና የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በዓሉን በሚመጥን መልኩ የተገነቡ የመንገድ፣ የስቴዲየም፣ የሆቴሎችና የሁነት ማሳያ ፕሮጀክቶች መሰረተ ልማቶችን በአጭር ጊዜ በጥራት ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ሲሉ ተናግረዋል። ክልሉ ቀኑን በድምቀት ማስተናገድ የሚያስችል በቂና የተሟላ ዝግጅት ማድረጉን መመልከታቸውን የጽህፈት ቤት ሀላፊው አስታውቀዋል።
ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል አማራጭ የሌለው መንገድ ነው
Nov 14, 2025 79
አዲስ አበባ፤ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት የሚያስገኝና አገርን ወደፊት የሚያራምድ አማራጭ የሌለው መንገድ ነው ሲሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። በሃይል አማራጭ ስልጣን ለመቆጣጠር የሚደረግ ትግል በየትኛውም የሕግ ማዕቀፍ ተቀባይነት የሌለውና በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑ ይነገራል። በኢትዮጵያ የቀደመ ታሪክ ስልጣንንም ሆነ የፖለቲካ ፍላጎትን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በውይይት ከመፍታት ይልቅ በሃይል አማራጭ ለማስፈጸም አዝማሚያዎች በተደጋጋሚ እንደሚታዩ የታሪክ ሰነዶች ያሳያሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ 328 ላይ የኃይል ፍላጎት ካልተገራ ሁሉን መጠቅለል እንደሚፈልግ ያነሳሉ። ይሄም በፖለቲካ ገበያው ላይ ትርምስ ይፈጥራል። የኃይል ፍሰትና ስበትም ይረበሻል። ትርምሱ ሥርዓትን ይበጠብጣል። በዚህም የኃይል ሞገዱ ማንን እንደሚያጠፋ መለየት እስኪያዳግት ድረስ ረብሻ እንደሚሆን አንስተዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገፅ 383 ላይ እንደተመላከተው፤ አሁን ባለችው ኢትዮጵያ የሀሳብ ገበያ ባህል እንዲሆን እየተሰራ ነው። ለዚህም መንግስት ሶስት መንገዶችን እየተከተለ ይገኛል። እነዚህም ሀገራዊ ምክክር፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክክርና የሕዝብ መድረኮች ናቸው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለህዝብ ጥቅምና ለአገር ዕድገት እንታገላለን የሚል አቋም ያለው ማንኛውም ቡድን ዓላማውን በሰላማዊ መንገድ ከማሳካት ውጪ አማራጭ የለውም ይላሉ። በተለይም መንግስት ለሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በሩን ክፍት ባደረገበት ወቅት ከሰላማዊ ትግል ውጭ ምንም አማራጭ እንደሌለ ያነሳሉ። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ቀጄላ መርዳሳ እንደሚሉት፤ መንግስት በሃይል አማራጭ ፍላጎታቸውን ለማሳካት የሚፈልጉ ቡድኖችን ወደ ሰላም መጥተው በጋራ እንዲሰሩ በተደጋጋሚ ጥሪ እያቀረበ ነው። ይህን ጥሪ ተቀብለው የመጡ በርካታ ሃይሎች ቢሆኑም አሁንም ድረስ የሰላም አማራጭን በመተው ወደ ኋላ የሸሹ መኖራቸውን አንስተዋል። የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አበራ በቀለ፣ በኢትዮጵያ በሃይል ፍላጎትን ለማሳካት መሞከር ጊዜው አልፎበታል ይላሉ። ማንም ቡድን ወይም ፖለቲካ ፓርቲ የሚፈልገውን የፖለቲካ ዓላማ ለማሳካት ከሰላም ውጪ ያለው አማራጭ ተቀባይነት የሌለው ነው ብለዋል። የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የውጭና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአገርን ሰላም ማረጋገጥ ለአንድ አካል የሚተው አለመሆኑን ያነሳሉ። የታጠቁ ሃይሎች አለን የሚሉትን ጥያቄ ወደ ውይይት እንዲያመጡ ተደጋጋሚ ጥሪ እየቀረበ መሆኑን አመልክተው፤ ለዚህም አገራዊ ምክክርን የመሰሉ አማራጮች መቅረባቸውን አንስተዋል። እንደ ተፎካካሪ ፓርቲዎቹ ገለጻ፤ የሰላማዊ ትግል አንዱ ዓላማ ለህዝብና ለአገር የሚጠቅሙ አጀንዳዎቸን መቅረጽና በሀሳብ ልዕልና መንግስት እንዲቀበለው ማስገደድ ነው። በአንዳንድ አካባቢዎች ፍላጎታቸውን በሃይል ለማሳካት የታጠቁ ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ሆነ ሌሎች ቡድኖች ወደ ሰላማዊ ትግል እንዲመለሱም ጥሪ አቅርበዋል።
በዓሉ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለመላው ዓለም የምናሳይበት ነው
Nov 14, 2025 69
አዲስ አበባ፤ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡-የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለመላው ዓለምና ለኢትዮጵያዊያን የምናሳይበት ነው ሲሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘው ተሻገር ገለፁ። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ይከበራል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የፌዴራል የበዓሉ አቢይ ኮሚቴ 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል ዝግጅትን ገምግሟል፡፡ በግምገማ መድረኩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘው ተሻገር፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የፌዴራል የበዓሉ አቢይ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል። በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የበዓሉ ሁነቶች የሚከናወንባቸው ስፍራዎች፣ የእንግዶች ማረፊያ ቦታዎች፣ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የከተሞች የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ያከናወናቸው የዝግጅት ስራዎች ተገምግሟል። በግምገማ መድረኩ እንግዶች የሚያርፋባቸው ሆቴሎች ተለይተው ደረጃቸውን አሟልተው መዘጋጀታቸው ተብራርቷል። እንዲሁም የሆሳዕና ከተማ ሲፖዚየም የሚካሄድበት አዳራሽ፣ በወልቂጤ ከተማ የንግድ ኤግዚብሽን እና ባዛር ስፍራ ግንባታ መጠናቀቁም ተመላክቷል፡፡ አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት፤የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዓሉን በባለቤትነት ይዞ በደመቀ ሁኔታ ለማክበር ጥሩ ዝግጅት ማድረጉ አንስተዋል። ያየናቸው የልማት ስራዎች የበዓሉ ትሩፋቶች መሆናቸውን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። በዓሉ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለመላው አለምና ለኢትዮጵያዊያን የምናሳይበት ነው ያሉት አፈ ጉባኤው በዓሉን በተሳካ ሁኔታ ለማክበር የሚያስችሉ ቀሪ ስራዎች እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። የህዝቡን አንድነት በማጠናከር የመቻቻል እና የመከባበር እሴቶች እንዲጎለብቱ በዓሉ የላቀ አስተዋጽኦ ያበረክታል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ናቸው። እንግዶችን በአግባቡ ተቀብሎ በዓሉ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን መሰረት አድርጎ እንዲከበር የክልሉ መንግሥትና ህዝብ በሁለንተናዊ መልኩ በቂ ዝግጅት ማድረጉን ገልፀዋል። ቀሪ የዝግጅት እና የልማት ስራዎችን በ15 ቀን ውስጥ ማጠናቀቅ እንደሚቻል አረጋግጠዋል። በዓሉ ከተስፋ ብርሃን ተሸጋግረን ወደ ሚጨበጥ ተስፋ ላይ መድረሳችንን የምናሳይበት ይሆናል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ በዓሉ የአብሮነታችንና የህብረ ብሔራዊ አንድነታችን ማሳያ በመሆኑ በድምቀት ለማክበር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ተብሏል። በበዓሉ ሲምፖዚየሞች፣ ባዛሮች፣ የውይይት መድረኮች እና የተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚካሄዱ ተጠቁሟል ።
በፖለቲካው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ ናቸው
Nov 14, 2025 73
አዲስ አበባ፤ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡-በፖለቲካው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ መሆናቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም መስከ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተጀመረው ጉዞ ማሳያ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ ናቸው፡፡ የጠላትና ወዳጅ ሆኖ የቆየው የፖለቲካ ሂደትን ለመቀየር ታሪካዊ እርምጃዎች መወሰዳቸወን ተናግረዋል። በፖለቲካው መስክ የነበረውን አግላይነት በማስቀረት ሁሉንም አሳታፊ በማድረግ እየተከናወኑ ያሉ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ስራዎች መኖራቸውንም ገልጸዋል፡፡ ለአብነትም 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በኃላ በመንግስት ምስረታ ሂደት ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አባላት በካቢኔ ውስጥ በማሳተፍ ለሀገር ዕድገት በጋራ እንዲሰሩ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ይህም በሀገር ደረጃ የመግባባት ዲሞክራሲን ለመገንባት የተጀመረው ሂደት በተግባር የተገለጸበት መሆኑን ጠቁመው፤ የተለያዩ አመለካከቶች የያዙ የኢትዮጵያ ልጆች በሀገራዊ ጉዳዮች በጋራ መስራት እንደሚችሉም ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ይህ ሂደትም ኢትዮጵያዊ መልክ ያለውና ኢትዮጵያዊ መግባባት ላይ የተመሰረተ ዲሞክራሲ ለመገንባት የተጀመረው ጥረት አካል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ታስቦ የተቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በፖለቲካው ዘርፍ እየተገኙ ከሚገኙ ስኬቶች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ብቻ ለመፍታት አቅጣጫ በማስቀመጥ ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑም ሌላኛው በፖለቲካ ዘርፍ ያለ ስኬት መሆኑን ጠቁመው የፕሪቶሪያው ስምምነትንም ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ ትጥቅ ያነገቡ ቡድኖች ሰላማዊ ፖለቲካን እንዲያራምዱ በሩ ክፍት መደረጉም የፖለቲካ ባህል እየተቀየረ ለመሆኑ ሌላኛው ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የተጀመረው የመንግስት ጥረት ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ ለአብነትም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በሶማሌና በሌሎችም ክልሎች የነበሩ ችግሮችን ሙሉ በሙሉ በመፍታት በክልሎቹ ሰላማዊ የልማት እንቅስቃሴ እንዲካሄድ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ከበርካታ የታጠቁ አካላት ጋር በመነጋገር ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመጡ መደረጉን ጠቁመው፤ በአማራ ክልልም የሰላም በር ተከፍቶ ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በለውጡ ሂደት በሁሉም መስክ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል መንግስት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
በመደመር መንግሥት ዕሳቤ ሁሉም ተቋማት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን የመተግበር ግዴታ አለባቸው
Nov 14, 2025 81
አዲስ አበባ፤ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡-በመደመር መንግሥት ዕሳቤ ሁሉም ተቋማት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን የመተግበር ግዴታ እንዳለባቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምፀሀይ ጳውሎስ አስታወቁ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የተሞክሮ ልውውጥ መድረክ እየተካሄደ ነው። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምፀሀይ ጳውሎስ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ሪፎርሙ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደርን በሚፈለገው ልህቀት ማስቀጠል የሚያስችል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የመደመር መንግሥት ዕይታ ለዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀው ስልጠና ወቅት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ሙሉ በሙሉ መጠናቀቅ እንዳለበት አቅጣጫ ማስቀመጣቸውን ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ ተቋማት ዘመናትን የሚሻገሩ ዘላቂና እኛን መምሰል አለባቸው በሚል በግልጽ መቀመጡን ገልጸዋል። በመሆኑም ሪፎርሙ በሀገራዊ ዕሳቤ የተቃኘ፣ ከሀገራዊ እሴት የተቀዳ መሆኑን አመልክተው፤ በሁሉም ተቋማት ገቢራዊ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል። ሪፎርሙ በሦስት ምዕራፎች ሲከፈል የተሻለ አፈፃፀም፣ መካከለኛና ወደኋላ የቀሩትን በመለየት መሆኑን አንስተው፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተሻለ አፈፃፀም አስመዝግቦ በግልጽ መመረጡን ተናግረዋል። የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙ በሶስት ምዕራፍ የተለየበት ሌላው መንገድ ተቋማት ከመጀመሪያዎቹ ልምድ እየወሰዱ በተሻለ መፈፀም እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። ሂደቱ በሰባቱ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ምሰሶዎች አኳያ መታየት እንዳለበት ጠቁመው፤ ሁሉም ተቋማት ተግባራዊ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ሪፎርሙ በዘመናት መካከል የፀና ተቋም የመገንባት ዓላማ መያዙን ገልጸው፤ ሪፎርሙን በሂደት ማሻሻልና ማሳለጥ ይገባል ብለዋል። በዚህም የመጀመሪያ ምዕራፍ ተቋማት ወደ ትግበራ፣ ሁለተኛ ምዕራፍ ላይ ያሉት ደግሞ ወደ ዝግጅት በፍጥነት መግባት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ለሪፎርሙ ስኬት ምቹ የሥራ ቦታ መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ የሰራተኛው ምዘና ከሥራው ዓይነትና ባህርይ ጋር የተጣጣመ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። ተቋማት የሰራተኞችን አቅም ለመለየት፣ ለመመዘንና ለማብቃት የሚያስችል ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸው፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሚከተለው አሰራር ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ምዘና ወቅት ስራውን በአግባቡ ሳይረዳ የሚሰራ ባለሙያ እንዳለ አረጋግጠናል ያሉት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትሯ፤ ምዘናው የሰራተኛውን ጉድለቶች ለይቶ መሙላት ታሳቢ ያደረገ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ከጎረቤቶቿ ጋር አብሮ የማደግ ፍላጎቷን ለማሳካት እየሰራች ነው - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)
Nov 14, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ከጎረቤት ሀገሮች ጋር አብሮ የማደግና የመበልጸግ ፍላጎቷን ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) አስታወቁ። "ሆርን ሪቪው" የተባለው ቲንክ ታንክ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ትናንት የፖሊሲ ፎረም አካሂዷል። በፎረሙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡና አጋር አካላትን ጨምሮ ፖሊሲ አውጪዎችና ምሁራን የታደሙ ሲሆን፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ(ዶ/ር) በአፍሪካ ቀንድ በተለይም በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም፤ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ግጭትና አለመረጋጋት ዋነኛ መገለጫ እየሆነ መጥቷል በሚል ከሁሉም የሚዲያ አማራጮች መስማት የተለመደ ነው። ቀጣናው ሰፊ የሚታረስ መሬት፣ የውሃ ሀብት፣ እምቅ የተፈጥሮ ማዕድንና ጠንካራ ሰራተኛ ሕዝብ ያለው መሆኑን አመልክተው፤ በአካባቢው በሚፈጠሩ ግጭቶች ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ አዳጋች እንዳደረገውም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ይህን ለረጅም ጊዜ የልማት፣ የሰላምና የደህንነት ስጋት የሆነውን ቀጣና ለመቀየር በመሰረተ ልማትና በኢኮኖሚ ትስስር እንዲፈጠር ጥረቶች እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ቅድሚያ ለጎረቤት የሚሰጥ፣ ከሁሉም ጋር በሰላማዊና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ አብሮ የመስራት ዓላማ መያዙን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገሮች ጋር በሰላማዊና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ አብሮ የማደግ ፍላጎቷን በመሰረተ ልማትና በኤሌክትሪክ ሃይል ትስስር በተግባር ማሳየቷንም አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት እያደገ ከመጣው የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር አኳያ እንዲሁም እየተመዘገበ ያለውን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስቀጠል የባህር በር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ ቀደም ባሉት ዓመታት የባህር በር የነበራት ሀገር ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንድታጣ መደረጉን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ እና ኤርትራ አንድ ሀገር እንደነበሩ ያስታወሱት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ በወቅቱ ኢትዮጵያን የመሩ መንግስታት ሃላፊነት በጎደለው መልኩ ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠልና ከባህር እንድትነጠል ማድረጋቸውን አመልክተዋል። በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ለዘመናት የዘለቀው ግጭት መነሻ ከድንበር ውዝግብና ከባህር በር ፍላጎት የተሻገረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የኢትዮጵያን የሰላምና የልማት ፍላጎት በየጊዜው የሚገዳደር መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኑን ያብራሩት ሚኒስትሩ፤ ሁሉም ሀገሮች ለዚህ ሊተባበሩ ይገባል ብለዋል። የውጭ ጣልቃ ገብነትን መከላከልና የንግድና ኢንቨሰትመንት ግንኙነትን ማሳደግ ለቀጣናዊ ኢኮኖሚ ውህደት መሳካት ወሳኝ መሆኑንም ነው ያነሱት። እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፤ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም ዘላቂ ልማትን ለማምጣት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፉን ማጠናከር አለበት። ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ከሰሩ ለሌሎች ሀገሮች ምሳሌ የሚሆን ትብብር መፍጠር እንደሚችሉም ተናግረዋል።
በሶማሌ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል
Nov 14, 2025 49
ጅግጅጋ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር ተገለጸ። በክልሉ አከባበሩን በተመለከተ የዝግጅቱ አብይ ኮሚቴ በአከባበሩ ዙሪያ ዛሬ ተወያይቷል። የሶማሌ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ መሀመድ አዳን እንደገለጹት በክልሉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል። በክልሉ በዓሉ በወረዳ፣ በዞንና በከተማ አስተዳደሮች ከዛሬ ጀምሮ እስከ ህዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም በደም ልገሳ፣ በንግድና ባዛር፣ በችግኝ ተከላ፣ በስፖርታዊ ውድድሮች፣ በፓናል ውይይት፣ አረጋውያንን በመደገፍና በሌሎች ዝግጅቶች እንደሚከበር ተናግረዋል። በክልል ደረጃ ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም በጅግጅጋ ከተማ የበዓሉ ማጠቃላይ ፕሮግራም እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለጋራ ልማትና ዕድገት በአንድነት እንድንተጋ መነሳሳትን ፈጥሯል - የመንግስት ሰራተኞች
Nov 14, 2025 53
ወልዲያ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለጋራ ልማትና ዕድገት ሁላችንም በህብረ ብሔራዊ አንድነት እንድንተጋ መነሳሳት ፈጥሮልናል ሲሉ የወልዲያ ከተማና የሰሜን ወሎ ዞን የመንግስት ሠራተኞች ተናገሩ። በአገራችን የሚከበረው 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ብሄራዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በወልዲያ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። ውይይቱ ላይ የተሳተፉ የመንግስት ሠራተኞች እንዳሉት፤ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለጋራ ልማትና ዕድገት በህብረ ብሔራዊ አንድነት እንድንተጋ መነሳሳትን ፈጥሯል። ከተሳተፊዎቹ መካከል አቶ ታምራት ወራሴ በዓሉ ስለ ህገ መንግስት፣ ዴሞክራሲና የፌደራል ስርዓት ፋይዳ ዙሪያ እውቀት እንድንጨብጥ አስችሎናል ብለዋል። የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች አገር የሆነችው ኢትዮጵያ የህዝቦቿ አንድነት ዛሬም በእኛ ዘመን ተጠናክሮ እንዲቀጥል የጋራ ትርክት ላይ በማተኮር መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል። ነጠላ ትርክትን በማስወገድ ለጋራ ልማትና ዕድገት በአንድነት ልንተጋ ይገባል ያሉት ደግሞ ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ጀማል ሙሐመድ ናቸው። የህገ-መንግስቱ መልካም ትሩፋቶች ለጋራ ተጠቃሚነታችን ፈር ቀዳጅ በመሆናቸው ተጠብቆ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ማዋል ይገባል ብለዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊና ውይይቱን የመሩት አቶ ፍስሃ መንግስቴ በበኩላቸው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀንን ስናከብር ለህዝቦች ሠላም፣ ፍቅርና አንድነት በመስራት መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። በዓሉን ስናከብር በህብረ ብሔራዊ አንድነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ሃገረ መንግስትን እውን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሊሆን ይገባልም ብለዋል። የዘንድሮውን በዓል ለየት የሚያደርገው የህዳሴ ግድባችን ባስመረቅንበት ማግስት የሚከበር በመሆኑ ደስታችንን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል ያሉት ደግሞ የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ አቶ ኢትዮጲስ አያሌው ናቸው። በዓሉን ስናከብርም በህብረ ብሔራዊ አንድነት የተገነባችውን ኢትዮጵያ ወደፊት ለማሻገር ቁርጠኛነታችንን በማረጋገጥ መሆን አለበት ብለዋል። በመድረኩ ላይም የወልዲያ ከተማ አስተዳደር፣ የሰሜን ወሎ ዞን የመንግስት ሠራተኞችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት "ዴሞክራሲና የኢትዮጵያ ፌደራል ስርዓት" በሚል ርእስ ውይይት አካሄደዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እንግዶቹን መቀበል የሚያስችል የተሟላ ዝግጅት አድርጓል - ምክር ቤቱ
Nov 14, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ለማክበር የሚመጡ እንግዶቹን ለመቀበል የተሟላ ዝግጅት ማድረጉን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ገለጹ። ምክትል አፈ ጉባኤዋ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአጭር ጊዜ በዓሉን ለማስተናገድ ያከናወነው ቅድመ ዝግጅት የሚደነቅ ነው። እንደ ክልል አብዛኛዎቹ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን አንስተው፤ ቀሪ ስራዎችን በቀሩት ጊዜያት እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል። በዓሉን የክልሉን ሁለንተናዊ አቅሞች ለማስተዋወቅ መጠቀም ይገባል ሲሉም ምክትል አፈ ጉባኤዋ አሳስበዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤት ሀላፊ ትግሉ መለሰ በበኩላቸው፤ ክልሉ በአጭር ጊዜ የመሰረተ ልማት ክፍተቶችን ለማሟላት ያደረገው ዝግጅት ሰፊና የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በዓሉን በሚመጥን መልኩ የተገነቡ የመንገድ፣ የስቴዲየም፣ የሆቴሎችና የሁነት ማሳያ ፕሮጀክቶች መሰረተ ልማቶችን በአጭር ጊዜ በጥራት ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ሲሉ ተናግረዋል። ክልሉ ቀኑን በድምቀት ማስተናገድ የሚያስችል በቂና የተሟላ ዝግጅት ማድረጉን መመልከታቸውን የጽህፈት ቤት ሀላፊው አስታውቀዋል።
ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል አማራጭ የሌለው መንገድ ነው
Nov 14, 2025 79
አዲስ አበባ፤ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት የሚያስገኝና አገርን ወደፊት የሚያራምድ አማራጭ የሌለው መንገድ ነው ሲሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። በሃይል አማራጭ ስልጣን ለመቆጣጠር የሚደረግ ትግል በየትኛውም የሕግ ማዕቀፍ ተቀባይነት የሌለውና በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑ ይነገራል። በኢትዮጵያ የቀደመ ታሪክ ስልጣንንም ሆነ የፖለቲካ ፍላጎትን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በውይይት ከመፍታት ይልቅ በሃይል አማራጭ ለማስፈጸም አዝማሚያዎች በተደጋጋሚ እንደሚታዩ የታሪክ ሰነዶች ያሳያሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ 328 ላይ የኃይል ፍላጎት ካልተገራ ሁሉን መጠቅለል እንደሚፈልግ ያነሳሉ። ይሄም በፖለቲካ ገበያው ላይ ትርምስ ይፈጥራል። የኃይል ፍሰትና ስበትም ይረበሻል። ትርምሱ ሥርዓትን ይበጠብጣል። በዚህም የኃይል ሞገዱ ማንን እንደሚያጠፋ መለየት እስኪያዳግት ድረስ ረብሻ እንደሚሆን አንስተዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገፅ 383 ላይ እንደተመላከተው፤ አሁን ባለችው ኢትዮጵያ የሀሳብ ገበያ ባህል እንዲሆን እየተሰራ ነው። ለዚህም መንግስት ሶስት መንገዶችን እየተከተለ ይገኛል። እነዚህም ሀገራዊ ምክክር፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክክርና የሕዝብ መድረኮች ናቸው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለህዝብ ጥቅምና ለአገር ዕድገት እንታገላለን የሚል አቋም ያለው ማንኛውም ቡድን ዓላማውን በሰላማዊ መንገድ ከማሳካት ውጪ አማራጭ የለውም ይላሉ። በተለይም መንግስት ለሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በሩን ክፍት ባደረገበት ወቅት ከሰላማዊ ትግል ውጭ ምንም አማራጭ እንደሌለ ያነሳሉ። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ቀጄላ መርዳሳ እንደሚሉት፤ መንግስት በሃይል አማራጭ ፍላጎታቸውን ለማሳካት የሚፈልጉ ቡድኖችን ወደ ሰላም መጥተው በጋራ እንዲሰሩ በተደጋጋሚ ጥሪ እያቀረበ ነው። ይህን ጥሪ ተቀብለው የመጡ በርካታ ሃይሎች ቢሆኑም አሁንም ድረስ የሰላም አማራጭን በመተው ወደ ኋላ የሸሹ መኖራቸውን አንስተዋል። የህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አበራ በቀለ፣ በኢትዮጵያ በሃይል ፍላጎትን ለማሳካት መሞከር ጊዜው አልፎበታል ይላሉ። ማንም ቡድን ወይም ፖለቲካ ፓርቲ የሚፈልገውን የፖለቲካ ዓላማ ለማሳካት ከሰላም ውጪ ያለው አማራጭ ተቀባይነት የሌለው ነው ብለዋል። የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የውጭና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአገርን ሰላም ማረጋገጥ ለአንድ አካል የሚተው አለመሆኑን ያነሳሉ። የታጠቁ ሃይሎች አለን የሚሉትን ጥያቄ ወደ ውይይት እንዲያመጡ ተደጋጋሚ ጥሪ እየቀረበ መሆኑን አመልክተው፤ ለዚህም አገራዊ ምክክርን የመሰሉ አማራጮች መቅረባቸውን አንስተዋል። እንደ ተፎካካሪ ፓርቲዎቹ ገለጻ፤ የሰላማዊ ትግል አንዱ ዓላማ ለህዝብና ለአገር የሚጠቅሙ አጀንዳዎቸን መቅረጽና በሀሳብ ልዕልና መንግስት እንዲቀበለው ማስገደድ ነው። በአንዳንድ አካባቢዎች ፍላጎታቸውን በሃይል ለማሳካት የታጠቁ ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ሆነ ሌሎች ቡድኖች ወደ ሰላማዊ ትግል እንዲመለሱም ጥሪ አቅርበዋል።
በዓሉ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለመላው ዓለም የምናሳይበት ነው
Nov 14, 2025 69
አዲስ አበባ፤ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡-የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለመላው ዓለምና ለኢትዮጵያዊያን የምናሳይበት ነው ሲሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘው ተሻገር ገለፁ። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ይከበራል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የፌዴራል የበዓሉ አቢይ ኮሚቴ 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል ዝግጅትን ገምግሟል፡፡ በግምገማ መድረኩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘው ተሻገር፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የፌዴራል የበዓሉ አቢይ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል። በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የበዓሉ ሁነቶች የሚከናወንባቸው ስፍራዎች፣ የእንግዶች ማረፊያ ቦታዎች፣ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የከተሞች የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ያከናወናቸው የዝግጅት ስራዎች ተገምግሟል። በግምገማ መድረኩ እንግዶች የሚያርፋባቸው ሆቴሎች ተለይተው ደረጃቸውን አሟልተው መዘጋጀታቸው ተብራርቷል። እንዲሁም የሆሳዕና ከተማ ሲፖዚየም የሚካሄድበት አዳራሽ፣ በወልቂጤ ከተማ የንግድ ኤግዚብሽን እና ባዛር ስፍራ ግንባታ መጠናቀቁም ተመላክቷል፡፡ አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት፤የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዓሉን በባለቤትነት ይዞ በደመቀ ሁኔታ ለማክበር ጥሩ ዝግጅት ማድረጉ አንስተዋል። ያየናቸው የልማት ስራዎች የበዓሉ ትሩፋቶች መሆናቸውን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። በዓሉ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለመላው አለምና ለኢትዮጵያዊያን የምናሳይበት ነው ያሉት አፈ ጉባኤው በዓሉን በተሳካ ሁኔታ ለማክበር የሚያስችሉ ቀሪ ስራዎች እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። የህዝቡን አንድነት በማጠናከር የመቻቻል እና የመከባበር እሴቶች እንዲጎለብቱ በዓሉ የላቀ አስተዋጽኦ ያበረክታል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ናቸው። እንግዶችን በአግባቡ ተቀብሎ በዓሉ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን መሰረት አድርጎ እንዲከበር የክልሉ መንግሥትና ህዝብ በሁለንተናዊ መልኩ በቂ ዝግጅት ማድረጉን ገልፀዋል። ቀሪ የዝግጅት እና የልማት ስራዎችን በ15 ቀን ውስጥ ማጠናቀቅ እንደሚቻል አረጋግጠዋል። በዓሉ ከተስፋ ብርሃን ተሸጋግረን ወደ ሚጨበጥ ተስፋ ላይ መድረሳችንን የምናሳይበት ይሆናል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ በዓሉ የአብሮነታችንና የህብረ ብሔራዊ አንድነታችን ማሳያ በመሆኑ በድምቀት ለማክበር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ተብሏል። በበዓሉ ሲምፖዚየሞች፣ ባዛሮች፣ የውይይት መድረኮች እና የተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚካሄዱ ተጠቁሟል ።
በፖለቲካው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ ናቸው
Nov 14, 2025 73
አዲስ አበባ፤ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡-በፖለቲካው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ መሆናቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም መስከ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተጀመረው ጉዞ ማሳያ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ ናቸው፡፡ የጠላትና ወዳጅ ሆኖ የቆየው የፖለቲካ ሂደትን ለመቀየር ታሪካዊ እርምጃዎች መወሰዳቸወን ተናግረዋል። በፖለቲካው መስክ የነበረውን አግላይነት በማስቀረት ሁሉንም አሳታፊ በማድረግ እየተከናወኑ ያሉ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ስራዎች መኖራቸውንም ገልጸዋል፡፡ ለአብነትም 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በኃላ በመንግስት ምስረታ ሂደት ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አባላት በካቢኔ ውስጥ በማሳተፍ ለሀገር ዕድገት በጋራ እንዲሰሩ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ይህም በሀገር ደረጃ የመግባባት ዲሞክራሲን ለመገንባት የተጀመረው ሂደት በተግባር የተገለጸበት መሆኑን ጠቁመው፤ የተለያዩ አመለካከቶች የያዙ የኢትዮጵያ ልጆች በሀገራዊ ጉዳዮች በጋራ መስራት እንደሚችሉም ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ይህ ሂደትም ኢትዮጵያዊ መልክ ያለውና ኢትዮጵያዊ መግባባት ላይ የተመሰረተ ዲሞክራሲ ለመገንባት የተጀመረው ጥረት አካል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ታስቦ የተቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በፖለቲካው ዘርፍ እየተገኙ ከሚገኙ ስኬቶች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ብቻ ለመፍታት አቅጣጫ በማስቀመጥ ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑም ሌላኛው በፖለቲካ ዘርፍ ያለ ስኬት መሆኑን ጠቁመው የፕሪቶሪያው ስምምነትንም ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ ትጥቅ ያነገቡ ቡድኖች ሰላማዊ ፖለቲካን እንዲያራምዱ በሩ ክፍት መደረጉም የፖለቲካ ባህል እየተቀየረ ለመሆኑ ሌላኛው ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የተጀመረው የመንግስት ጥረት ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ ለአብነትም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በሶማሌና በሌሎችም ክልሎች የነበሩ ችግሮችን ሙሉ በሙሉ በመፍታት በክልሎቹ ሰላማዊ የልማት እንቅስቃሴ እንዲካሄድ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ከበርካታ የታጠቁ አካላት ጋር በመነጋገር ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመጡ መደረጉን ጠቁመው፤ በአማራ ክልልም የሰላም በር ተከፍቶ ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በለውጡ ሂደት በሁሉም መስክ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል መንግስት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
በመደመር መንግሥት ዕሳቤ ሁሉም ተቋማት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን የመተግበር ግዴታ አለባቸው
Nov 14, 2025 81
አዲስ አበባ፤ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡-በመደመር መንግሥት ዕሳቤ ሁሉም ተቋማት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን የመተግበር ግዴታ እንዳለባቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምፀሀይ ጳውሎስ አስታወቁ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የተሞክሮ ልውውጥ መድረክ እየተካሄደ ነው። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምፀሀይ ጳውሎስ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ሪፎርሙ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደርን በሚፈለገው ልህቀት ማስቀጠል የሚያስችል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የመደመር መንግሥት ዕይታ ለዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀው ስልጠና ወቅት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ሙሉ በሙሉ መጠናቀቅ እንዳለበት አቅጣጫ ማስቀመጣቸውን ገልጸዋል። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ ተቋማት ዘመናትን የሚሻገሩ ዘላቂና እኛን መምሰል አለባቸው በሚል በግልጽ መቀመጡን ገልጸዋል። በመሆኑም ሪፎርሙ በሀገራዊ ዕሳቤ የተቃኘ፣ ከሀገራዊ እሴት የተቀዳ መሆኑን አመልክተው፤ በሁሉም ተቋማት ገቢራዊ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል። ሪፎርሙ በሦስት ምዕራፎች ሲከፈል የተሻለ አፈፃፀም፣ መካከለኛና ወደኋላ የቀሩትን በመለየት መሆኑን አንስተው፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተሻለ አፈፃፀም አስመዝግቦ በግልጽ መመረጡን ተናግረዋል። የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙ በሶስት ምዕራፍ የተለየበት ሌላው መንገድ ተቋማት ከመጀመሪያዎቹ ልምድ እየወሰዱ በተሻለ መፈፀም እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል። ሂደቱ በሰባቱ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ምሰሶዎች አኳያ መታየት እንዳለበት ጠቁመው፤ ሁሉም ተቋማት ተግባራዊ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ሪፎርሙ በዘመናት መካከል የፀና ተቋም የመገንባት ዓላማ መያዙን ገልጸው፤ ሪፎርሙን በሂደት ማሻሻልና ማሳለጥ ይገባል ብለዋል። በዚህም የመጀመሪያ ምዕራፍ ተቋማት ወደ ትግበራ፣ ሁለተኛ ምዕራፍ ላይ ያሉት ደግሞ ወደ ዝግጅት በፍጥነት መግባት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ለሪፎርሙ ስኬት ምቹ የሥራ ቦታ መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ የሰራተኛው ምዘና ከሥራው ዓይነትና ባህርይ ጋር የተጣጣመ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። ተቋማት የሰራተኞችን አቅም ለመለየት፣ ለመመዘንና ለማብቃት የሚያስችል ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸው፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሚከተለው አሰራር ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ምዘና ወቅት ስራውን በአግባቡ ሳይረዳ የሚሰራ ባለሙያ እንዳለ አረጋግጠናል ያሉት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትሯ፤ ምዘናው የሰራተኛውን ጉድለቶች ለይቶ መሙላት ታሳቢ ያደረገ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
ማህበራዊ
የትምህርት ጥራትን አግባብነትና ፍትኃዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው
Nov 14, 2025 40
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ የትምህርት ጥራትን፣ አግባብነትንና ፍኃዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። ቋሚ ኮሚቴው የትምህርት ሚኒስቴርን የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል። የትምህርት ሚኒስቴር ስትራቴጂክ ጉዳየች ስራ አስፈጻሚ እሸቱ ገላዬ ሪፖርቱን ባቀረቡበት ወቅት በበጀት አመቱ ሶስት ወራት የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎች መከናወናችውን ተናግረዋል። በተለይ በትምህርት ትውልድ ንቅናቄ እንዲሁም ፈተናዎችን በኦንላይን ለመስጠት እየተሰራ ያለውን ስራን ለአብነት አንስተዋል፡፡ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መንግስት የትምህርት ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጡ ስራዎችን በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የትምህርት ቤቶችንና የመምህራንን አቅም ማሳደግን ጨምሮ ሌሎች በዘርፉ ስኬት ሊያመጡ የሚችሉ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተከናወኑት ተግባራትም ውጤት እየታዩ መሆናቸውንም አንስተዋል፡፡ እየተቀየረ ያለው የትምህርት አቅጣጫ ውጤታማ ዜጋ የሚፈጠር በመሆኑ ሁሉም ዜጋ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባው አክለዋል። በግምገማው የቋሚ ኮሚቴው አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን በፕሮጀክት ግንባታ እና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ራስ ገዝነት ዙሪያ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ወደ ራስ ገዝነት ለማስገባት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከፕሮጀክት አፈጻጸም አኳያም የተመረጡ ፕሮጀክቶችን ለማስፈጸም በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) የትምህርት ቤቶች ደረጃ ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ገልጸዋል፡፡ የ12ኛ ክፍል ውጤትን ለማሻሻል በየደረጃው እየተከናኑ የሚገኙ የክትትልና የቁጥጥር ስራዎች በልዩ ትኩረት መሠራት እንዳለባቸው ጠቁመው፤ ምንም ተማሪ ያላሳለፉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን አቅም ለማሳደግ በትኩረት መሰራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል፡፡ በአጠቃላይ የትምህርት ጥራትን አግባብነትና ፍትሃዊነትን የማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ጠይቀዋል፡፡
በመንግሥት በሕዝብ እና በባለሀብቶች የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን መደገፍ የምንፈልገውን ብልጽግና ለማምጣት ያስችላል
Nov 14, 2025 42
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በመንግሥት፣ በሕዝብ እና በባለሀብቶች የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን መደገፍ እና መንከባከብ የሚፈለገውን ብልጽግና ለማምጣት እንደሚያስችል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ያለ ዕውቀት የሚሠራ ሀገር የለም በሚል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ከሐይቅ የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት ጎን ለጎን በባለሀብቱ በላይነህ ክንዴ የተገነባውን "ገበታ ለትውልድ ሐይቅ ቁጥር 1 አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት" መመልከታቸውን ገልጸዋል። የፈረሰው የጭቃ ትምህርት ቤት ይሠራልን ብሎ የአካባቢው ማኅበረሰብ ለዓመታት የጠየቀውን ጥያቄ አቶ በላይነህ ክንዴ እንደመለሱ ጠቅሰው ለዚህም ላቅ ያለ ምስጋናዬን ማቅረብ እወዳለሁ ብለዋል። ልማት ውጤቱ መልከ ብዙ ነው። በአንድ አካባቢ የሚደረግን ማንኛውንም ዓይነት ልማት ከደገፍነውና ከተንከባከብነው አካባቢውን በአንድም በሌላም መንገድ ይቀይረዋል ነው ያሉት። የሐይቅ አካባቢ ሕዝብ የሚሠራውን የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት በመደገፉና ሰላሙን በማስከበሩ የትምህርት ቤት ግንባታውን ማስጨመሩን አመልክተዋል። ዛሬ ከአብርሆት ቤተ መጻሕፍት የተገኙ 4 ሺህ 250 መጻሕፍት ለትምህርት ቤቱ ቤተ መጻሕፍት ማስረከባቸውን የጠቆሙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም የልማቱና የሰላሙ ትሩፋት ነው ሲሉ ተናግረዋል። በየአካባቢው በመንግሥት፣ በሕዝብ እና በባለሀብቶች የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን በመንከባከብ፤ በመደገፍ፣ ዕንቅፋቶችን በማንሳት እና እንዲሳኩ ከጎናቸው በመቆም ባለ ብዙ አትራፊዎች መሆን እንችላለን ብለዋል። እንደ አቶ በላይነህ ክንዴ ያሉ ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን በመወጣት ማኅበራዊ ችግሮችን የሚፈቱ ባለ ሀብቶች በበዙ ቁጥር ብልጽግናችን ፈጣን ይሆናል ሲሉም ነው የገለጹት። እንደ ሐይቅ አካባቢ ሕዝብ ልማትና ሰላምን የሚከባከብ ማኅበረሰብ እየበዛ በመጣ ቁጥር ችግሮች ታሪክ ይሆናሉ ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
በክልሉ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ የተማሪዎችን መጠነ ማለፍ ለማሳደግ በትኩረት ተሰርቷል
Nov 14, 2025 59
ቡታጅራ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ የተማሪዎችን መጠነ ማለፍ ለማሳደግ በትኩረት መሰራቱን የክልል ትምህርት ቢሮ ገልጿል። የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር በበኩሉ ለትምህርት ጥራትና ለመምህራን መብት መከበር የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አስታውቋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር 2ኛ ዙር የትምህርት ጥራት ኮንፍረንስና የመምህራን ቀን በቡታጀራ ከተማ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አስከብር ወልዴ በክልሉ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ የተማሪዎችን መጠነ ማለፍ ለማሳደግ ተሰርቷል ብለዋል። መምህራን በስነ-ምግባር የታነፀ፣ ብቁና ሀገር ወዳድ ዜጋ ለማፍራት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። ባለፉት ሁለት ዓመትት የመምህራንን አቅም በማጎልበት በኩል ሰፋፊ ስራዎች መከናወናቸውንና በዚህም ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቁመዋል። መምህራን የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅም እንዲያገኙ በተሰራው ስራም ውጤት መገኘቱን ምክትል ቢሮ ሀላፊው ተናግረዋል። በመድረኩ የተገኙት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት ዮሃንስ በንቲ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በእውቀት እና በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ ለመቅረፅ በሚደረገው ጥረት የመምህራን አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ለስኬታማነቱም ማህበሩ የመምህራንን እውቀትና ክህሎት በማጎልበት ለትምህርት ጥራትና መብታቸውን ለማስከበር የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አንስተዋል። ማህበሩ የመምህራንን መብት በማስከበር እንዲሁም ዕውቀትና ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት በርታ ያረቢ ናቸው። ማህበሩ የተጀመረውን የትምህርት ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም አክለዋል፡፡ ለትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ውጤታማ አስተዋፅኦ ላበረከቱ መምህራን፣ ወላጆች፣ ተማሪዎችና ባለድርሻ አካላት እውቅና በየጊዜው እየተሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል። በኮንፍረንሱ በክልሉ በትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት ላይ ያተኮረ ጥናት ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን የተሻለ አፈፈፃፀም ያስመዘገቡ መምህራን፣ ውጤታማ ተማሪዎችና ወላጆች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በአማራ ክልል በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከስድስት ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ ሆነዋል
Nov 14, 2025 50
ደሴ፤ ሕዳር 5/2018(ኢዜአ)፡ - በአማራ ክልል በክረምት የጤና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከስድስት ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው "በጎነት ለጤናችን" በሚል መሪ ሃሳብ የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ ማጠቃለያ፣ የበጋ ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያና የእውቅና አሰጣጥ መድረከ በደሴ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የቢሮ ኃላፊው አቶ አብዱልከሪም መንግሥቱ እንደተናገሩት፤ በመደበኛ ከሚሰጠው የሕክምና አገልግሎት በተጨማሪ በክረምቱ በተካሄደው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በአነስተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል። ይህም ከፍለው መታከም የማይችሉ ከ6ሚሊዮን በላይ ሰዎች የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግና ከ82 ሺህ ዩኒት በላይ ደም መሰብሰብ ተችሏል ብለዋል። በክረምቱ የተገኘውን ተሞክሮ በማስፋት በበጋው ወራትም ተግባሩ ተጠናክሮ እንዲቀጠል የጤና ባለሙያዎችና ሕብረተሰቡን በማስተባበር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአገልግሎቱ እስከ ከፍተኛ ቀዶ ሕክምና ጭምር መስጠት መቻሉን ጠቁመው፤ ለዚህም በየደረጃው የሚገኙ የጤና ባለሙያዎችና ጤና ተቋማት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የሰሜን ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋ ሞላ በበኩላቸው፤ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የጤና ተቋማትና ጤና ባለሙያዎችን በማስተባበር ለበርካታ አቅመ ደካሞች ሕክምና በነጻ መሰጠቱን ተናግረዋል። በክረምት የተገኘውን ልምድና ተሞክሮ በበጋው ወራትም ለማስቀጠል ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። በደሴ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የሕክምና ተሃድሶና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አስተባባሪ ሲስተር ውብእጅግ ወርቅነሕ እንዳሉት፤ በክረምቱ የጤና በጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማው ከ16 ሺህ በላይ ሰዎች ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል። አገልግሎቱን በበጋውም ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል የተሰጠን እውቅና የሚያነሳሳ ነው ብለዋል። በእውቅና አሰጣጡ መድረክ ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደረ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
ለብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከባበር በመሰረተ ልማት አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ነው - የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር
Nov 14, 2025 48
ሆሳዕና፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሆሳዕና ከተማ ለሚከበረው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በመሰረተ ልማት አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። 20ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለሀብረብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ይከበራል። በዓሉ በፌደራል ደረጃ በሚከበርበት ሆሳዕና ከተማ ከማክበሪያ ስፍራና እንግዶች ማረፊያ ጀምሮ የተለያዩ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው። በዝግጅት ምዕራፍ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች በዋናነት ይጠቀሳሉ። የሆሳዕና ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ዕህፈት ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ተከተል ጩፋሞ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በከተማው በፌዴራልና በከተማ አስተዳደሩ ከ30 ኪሎ ሜትር በላይ የአስፓልት መንገድ ሥራ እየተከናወነ ነው፡፡ በከተማ አስተዳደሩ በመጀመሪያ ምዕራፍ የ12 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነና ልማቱ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ከተማዋን ተወዳዳሪና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚገነቡ የመሰረተ ልማት ሥራዎች የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀን በዓልን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይ የመንገድ መሰረተ ልማቱን ከበዓሉ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ትኩረት መሰጠቱን ነው ያመለከቱት። በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሶዶና አካባቢው ፕሮጀክቶች ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ሰለሞን ሞላ በበኩላቸው እንዳሉት ተቋሙ በራሱ ወጪ በከተማው የ10 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ያከናውናል። የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ አካል የሆነው የ4 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራን በተያዘው ወር መጨረሻ በማጠናቀቅ ለበዓሉ ለማድረስ ርብርብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የኮሪደር ልማቱ ሥራው የተሽከርካሪና የእግረኛ መንገዶችን ጨምሮ የመዝናኛ፣ የአረንጓዴ ስፍራዎች፣ የመንገድ አካፋይና መብራቶችን ባካተተ መልኩ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የመሳይ ኦሊ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ የሆሳዕና ከተማ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ታደሰ አማኑኤል በበኩላቸው፣ ልማቱን በታቀደው ጊዜ ለማጠናቀቅ ቀንና ማታ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የኮሪደር ልማት ሥራውን ለኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ለማድረስ በርብርብ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል። በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ከተማዋን ለነዋሪው ምቹ ከማድረግ ባለፈ ከአቻ ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ የሚያደርጋት ነው ያሉት ደግሞ የከተማው ነዋሪ እሸቱ ኃይሌ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በከተማው መከበር የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተናግረዋል፡፡
ቅርሶችን በመጠበቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸውን ለማጎልበት የተሰሩ ተግባራት አበረታች ውጤቶች እያስገኙ ነው
Nov 14, 2025 54
ድሬዳዋ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ ቅርሶችን በመጠበቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸውን ለማጎልበት የተሰሩ ተግባራት አበረታች ውጤቶች እያስገኙ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ህይወት ኃይሉ ተናገሩ። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን " በተቀናጀ ትብብር ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውርን እንከላከል " በሚል መሪ ሃሳብ ህገ- ወጥ የቅርስ ዝውውር መከላከል ዓለምአቀፍ ቀንን ዛሬ በድሬዳዋ በውይይት አክብሯል ። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ህይወት ኃይሉ በወቅቱ እንዳሉት ቅርሶችን በመጠበቅ ለአገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚያበረክቱትን ፋይዳ ለማጎልበት የተሰሩ ተግባራት አበረታች ውጤቶች እያስገኙ ነው። ቅርሶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመመዝብ፣ ደረጃ በማውጣትና በማልማት ሁለንተናዊ አብርክቷቸውን እውን ለማድረግ በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በፌደራልም ሆነ በክልሎች የሚገኙ ቅርሶች ላይ ምርምሮችና ዕድሳትን በማካሄድ ቅርሶቹ ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉም እየተሰራ መሆኑን አክለዋል። በተለይ ከለውጡ በኃላ ለቅርሶች ጥበቃና እድሳት ልዩ ትኩረት በመስጠት ለቱሪስት መዳረሻ እንዲያገለግሉ መደረጉን አንስተዋል። በጅማ አባጅፋር፣ በጎንደር፣ በሶፍ ኡመር ዋሻ እና በሌሎች ቅርሶች ላይ የተሰሩ ስራዎችንም በማሳያነት አቅርበዋል። ከእድሳትና ጥበቃ በሻገርም በተለያዩ ወቅቶች በህገ ወጥ መንገድ ከአገር የወጡ 44 ቅርሶችን ከቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ጋር በመቀናጀት ማስመለስ መቻሉን ተናግረዋል ። እነዚህን አበረታች ስራዎች ለማጠናከርና ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውርን ለመከላከል ከአየር መንገድ፣ ከጉምሩክ፣ ከፍትህና ፀጥታ ፣ ከኃይማኖት አባቶች ጋር ዛሬ የተካሄደው ውይይት አጋዥ እንደሚሆን ጠቁመዋል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የድሬዳዋ አስተዳደር የባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ በበኩላቸው ከባለስልጣኑ ጋር በመቀናጀት ቅርሶችን የመጠበቅ፣ የማልማት፣ የማደስና የመመዝገብ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል። በተለይ ባለስልጣኑ፣ የ16ተኛዉ ክፍለ ዘመን የስልጣኔ አምባ የነበረውን የሐርላ መካነ ቅርስ እና 130 አመታት ያስቆጠረው የባቡር ተርሚናል በተገቢው መንገድ በማደስ ለቱሪስት መዳረሻነት እንዲውሉ መደረጉ ከዘርፉ የተሻለ ጥቅም እንዲገኝ መደላድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል። እነዚህን ሃብቶች በተገቢው መንገድ መጠበቅና መንከባከብ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን ገልጸዋል ። የተካሄደው የግንዛቤ ማጎልበቻ ውይይት በዘርፉ የተጀመሩ አበረታች ስራዎችን ተቀናጅቶ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የማዕድን ጸጋዎችን ለማልማት ወሳኝ አቅም ፈጥሯል
Nov 14, 2025 50
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የማዕድን ጸጋዎችን ለማልማት ወሳኝ አቅም መፍጠሩን በ4ኛው ዓለም አቀፍ የማዕድንና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ ተሳታፊ አልሚዎች ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 4ኛውን ዓለም አቀፍ የማዕድንና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ(MINTEX Ethiopia 2025) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መርቀው ከፍተዋል። ከኅዳር 4 እስከ 7/2018 ዓ.ም በሚቆየው ኤክስፖ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ውስጥና የውጭ አልሚ ባለሃብቶችን፣ ቴክኖሎጂ አምራቾች፣ ምሁራን እና አጋሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። የኤክስፖው ተሳታፊ የሀገር ውስጥና የውጭ አልሚዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ የኢንቨስትመንት አቅምን ለማስፋት አበረታች የልማት ምኅዳር መፈጠሩን ገልጸዋል። የአኮቦ ሚኒራልስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጆርገን ኤቭጀን፤ የማዕድን ኤክስፖው ምርትና አገልግሎታቸውን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ለማዕድን ዘርፍ የኢንቨስትመንት ከባቢ የፈጠረው የማበረታቻ ምኅዳር የወርቅ ማዕድን ልማት ስራን ለማስፋት አቅም እየፈጠረላቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሌላኛው የጂ.ሲ.ኤል ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሊ ጂያንጁን በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ የተፈጠረው ምቹ የኢንቨስትመንት ምኅዳር ሀገሪቱን ተመራጭ የልማት መዳረሻ እያደረጋት ነው ብለዋል። ድርጅታቸው በኢትዮጵያ ከአሥር ዓመታት በላይ ያደረገው የነዳጅ ፍለጋ ፍሬ አፍርቶ የተፈጥሮ ጋዝ በማስመረቅ ሁለተኛውን ምዕራፍ ግንባታ እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ማዕድን ሃብት ጸጋዎችና ምቹ ኢንቨስትመንት መዳረሻነትን በመጠቀም ግዙፉ የድፍድፍ ነዳጅ ማጣሪያ ግንባታ ላይ እንዲገቡ ማስቻሉን ተናግረዋል። በቀጣይም የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ምርት ልማት አቅምን በማሳደግ ኢትዮጵያን የኃይል አቅርቦት ማዕከል ለማድረግ በትጋት እንደሚሰሩ አስረድተዋል። የኢምራን ጂምስቶን ዋና ዳይሬክተር ቢኒያሚን አቡበከር፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ባለሃብቶች የሚሰጠው ድጋፍ በማዕድን ልማት ከፍተኛ መነቃቃት እየፈጠረ ነው ብለዋል። ለማዕድን አልሚዎች የተፈጠረው ምቹ የኢንቨስትመንት ምኅዳር ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የማዕድን ፍለጋ ልማት ስራን የሚያከናወኑበት ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። በማዕድን ልማት ለተሰማሩ አልሚዎች የሚሰጠው የፋይናንስ አቅርቦት ከፍተኛ ዕድገት እያስመዘገበ ነው ያሉት ደግሞ በዳሸን ባንክ የማርኬቲንግ ክፍል የሽያጭ ኃላፊ ነጋ ሽባባው ናቸው። በቀጣይም የኢትዮጵያን የማዕድን ሃብት ልማት ለማጠናከር የከበሩ ማዕድናት ካዝናን ጨምሮ የውጭ ምንዛሬ የገንዘብ አቅርቦት የማመቻቸት ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
የባሌ ዞን የቱሪስት መዳረሻዎች ልማት የቱሪስት ፍሰቱ እንዲጨምር አድርጓል
Nov 14, 2025 102
ሮቤ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በባሌ ዞን የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስተዋወቅ የተሰሩ ተግባራት የቱሪስት ፍሰቱ እንዲጨምር ማድረጋቸውን የዞኑ ቱሪዝም ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ በቱሪስቶች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የተሰማሩ ነዋሪዎችና ማህበራትም ከዘርፉ ተጠቃሚነታቸው ማደጉን ገልጸዋል። በጽህፈት ቤቱ የቱሪዝም ልማትና ማስፋፊያ ቡድን መሪ ሽብሩ አብዶ ለኢዜአ እንደተናገሩት የዞኑን የቱሪስት መስህቦች በማልማትና በማስተዋወቅ የዘርፉን አኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ለማሳደግ እየተሰራ ነው። ይህም ዞኑን የሚጎበኙ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች ቁጥር እንዲጨምር በማድረጉ በበጀት አመቱ የመጀመሪያው ሩብ አመት 16ሺህ 217 ቱሪስቶች መዳረሻዎቹን ጎብኝተዋል ብለዋል፡፡ መስህቦቹን የጎበኙት ቱሪስቶች ቁጥር ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነጻጸር በ15 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን አመልክተዋል። የቱሪስት መዳረሻ ልማቱ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ከማሳደግ ባለፈ የአካባቢውን ባህል ለማስተዋወቅና በዘርፉ ለተሰማሩ አካላት ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አክለዋል። ለአብነትም በሩብ አመቱ አካባቢውን ከጎበኙ ቱሪስቶች ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን በማሳያነት አንስተዋል። ለቱሪስቶች ቁጥር መጨመር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በአካባቢው እየተከናወኑ ያሉ መሰረተ ልማቶች እና አካባቢውን ለማስተዋወቅ የተደረጉ የተቀናጁ ጥረቶች እና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በዩኔስኮ በቋሚ ቅርስነት መመዝገብ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። በቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል በሮቤ ከተማ የቱሉ ሀምበላት የባህል ልብስ ቤት ተወካይ ወይዘሮ መርየማ ከድር ባሌ ሮቤን ለሚጎበኙ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ቱሪስቶች የባህል አልባሳት እንደሚሸጡ ተናግረዋል። የቱሪስቶች ቁጥር መጨመርና በተለያዩ ዲዛይኖች የሚያዘጋጁት የባህል አልባሳት ጥራት በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ማገዙን አስረድተዋል። የባሌ ፓርክን በአስጎብኚነትና በመንገድ በመምራት አገልግሎት የተሰማራው የዋሊያ ኢኮ-ቱሪዝም ማህበር ስራ አስኪያጅ ጃፈር መሐመድ በበኩሉ ፓርኩን ለማልማት የተደረገውን ጥረት ተከትሎ የጎብኚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። ይህም የማህበሩ አባላትም መንገድ በመምራት፣ ፈረስ በማከራየት የሚያገኙት ገቢ እንዲጨምር ማድረጉን ተናግረዋል። በባሌ ዞን በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት/ዩኔስኮ/ በአለም የተፈጥሮ ቅርስነት የተመዘገበውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን ጨምሮ ሌሎች ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ መስህቦች ይገኛሉ።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ተቋርጦ የነበረው የቴሌቪዥን ስርጭት ተመለሰ
Nov 14, 2025 32
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ተቋርጦ የነበረው የቴሌቪዥን ስርጭት ተመልሷል። የሳተላይት አቅራቢ ድርጅት በሆነው SES የቴሌ ፖርት ላይ እስራኤል አካባቢ ባጋጠመው ከፍተኛ የአየር ፀባይ ለውጥ ምክንያት የኃይል መቋረጥ ተፈጥሮ ነበር፡፡ በዚሁ ምክንያት ኢቢሲ ፤የፋና ቴሌቪዥን እና የአብዛኛዎቹ የሀገራችን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ስርጭት ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፤ አገልግሎቱን ለመመለስ በተሰራው ሥራ የቴሌቪዥን ስርጭቱ ተመልሷል።
በሳተላይት ችግር ምክንያት የቴሌቪዥን ስርጭት መቋረጥ አጋጥሟል
Nov 14, 2025 43
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 5/2018(ኢዜአ)፦የሳተላይት አቅራቢ ድርጅት በሆነው SES የቴሌ ፖርት ላይ እስራኤል አካባቢ ባጋጠመው ከፍተኛ የአየር ፀባይ ለውጥ ምክንያት የኃይል መቋረጥ መፈጠሩን ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ገለጸ፡፡ በዚሁ ምክንያት የፋና ቴሌቪዥን እና የፋና ፕላስ እንዲሁም የአብዛኛዎቹ የሀገራችን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ስርጭት ተቋርጧል፡፡ አገልግሎቱን ለመመለስ እየተሰራ በመሆኑ በትዕግስት እንዲጠብቁም ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን አስታውቋል።
ኢንተርፕርነርሽፕ ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ አቅም ጥቅም ላይ እንድታውል እያደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
Nov 14, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ ኢንተርፕርነርሽፕ ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ አቅም ጥቅም ላይ እንድታውል እያደረገ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ከህዳር 8 እስከ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደውን ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም መንግስት የኢንተርፕርነርሽፕ ሥራን ለማስፋት ቁርጠኛ በመሆኑ ዘርፉ ትልቅ ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አመራር የማይበገር ሀገር ለመገንባት ለዘርፉ ትኩረት በመስጠቱ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። ኢንተርፕርነርሽፕ ከሥራ ፈጠራና የሰው ሀይል ልማት ባለፈ ሀገር የመገንባት ጉዳይ መሆኑንም አንስተዋል። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ ተቋማት እሴት መፍጠር እንዳለባቸው ያምናል ያሉት ሚኒስትሯ፤ በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተመዘገበው ለውጥ ማሳያ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የኢንተርፕርነርሽፕ ዘርፉን ማገዝ እንደሚገባ በመጠቆም፤ የዘንድሮው የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት እንደሀገር ከያዝነው እሳቤ ጋር ይጣጣማል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ጉዞ ተጀምሯል ያሉት ሚኒስትሯ፣ በእስከ አሁን የተመዘገቡና የታዩ ለውጦች እንደምንችል ማሳያ ናቸው ነው ያሉት። ጉዟችን የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና እስከሚረጋገጥ በመሆኑ ረጅሙን ጉዞ በፈጠራና ኢንተርፕርነርሽፕ ማገዝ ይገባል ብለዋል። ዓለም አቀፉ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ከህዳር 8 ቀን ጀምሮ ለአስር ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ሁነቶች እንደሚካሄድም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በኢንተርፕርነርሽፕ ግዙፍ መሆኗን በማንሳት ይህም በዘርፉ በዓለም ሥነ ምህዳር ኢትዮጵያ የሚታይ ስራ እንዳላት ያመለክታል ብለዋል። መርሀ ግብሩ በዘርፋ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው መስራት የሚፈልጉ ተቋማትን የምናገኝበት ይሆናል ያሉ ሲሆን የስታርታፕ አዋጁን ጨምሮ የተወሰዱ እርምጃዎች መንግስት ለዘርፉ እድገት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ያመላክታል ነው ያሉት።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል-ተገልጋዮች
Nov 12, 2025 126
ሆሳዕና ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ማዕከል ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ሥራ መጀመሩ ይታወቃል። የማዕከሉን የሥራ እንቅስቃሴ በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር በስፍራው በመገኘት ተገልጋዮችና የሚመለከታቸውን የሥራ ሃላፊዎች አነጋግሯል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ዳንኤል በየነ፣ አቶ ደስታ ኤርቻዮ እና አቶ ደመቀ ሙሉነህ ፤ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። አገልግሎቱ በአንድ ማዕከል በርካታ ጉዳዮችን ጨርሶ መውጣት ከማስቻሉ ባለፈ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም መሰል የአገልግሎት ማዕከላትን በማስፋት በተገልጋዮች ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት እና የብልሹ አሰራር መንስኤዎችን ማስቀረት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ሻሜቦ፤ በማዕከሉ የተለያዩ ተቋማት 20 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶች እየሰፋ ይሄዳሉ ብለዋል። በማዕከሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት እያስቻለ በመሆኑ በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል።
ስፖርት
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና ሁለተኛ ድሉን አሳክቷል
Nov 14, 2025 36
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የስድስተኛ ሳምንት ጨዋታ ሲዳማ ቡና አዲስ አበባ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ምትኬ ብርሃኑ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥራለች። የግቦቹ ባለቤት የሆነችው ምትኬ ብርሃኑ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። ውጤቱን ተከትሎ ሲዳማ ቡና በዘጠኝ ነጥብ ደረጃውን ከስድስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አዲስ አበባ ከተማ በሶስት ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቀን ላይ በተደረገ ጨዋታ የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሃዋሳ ከተማን 3 ለ 2 አሸንፏል።
ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መሪነቱን ያጠናከረበትን ድል አስመዘገበ
Nov 14, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የስድስተኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሃ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሃዋሳ ከተማን 3 ለ 2 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዳግማዊት ሰለሞን በጨዋታ እና ፍጹም ቅጣት ምት ሁለት ግቦችን ስታስቆጥር ማህሌት ምትኩ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ፀሐይነሽ ጁላ እና የምስራች ላቀው ለሃዋሳ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ማህሌት ምትኩ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። ድሉን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ18 ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። ሃዋሳ ከተማ በ12 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። የኢትዮ ኤሌክትሪኳ ዳግማዊት ሰለሞን በሊጉ ከመረብ ላይ ያሳረፈቻቸውን ግቦች ወደ 11 ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት መሪነቷን አጠናክራለች። በአሁኑ ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ሲዳማ ቡና ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛል።
የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከሃዋሳ ከተማ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
Nov 14, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የስድስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ሁለት ጨዋታዎች በአበባ ቢቂላ ስታዲየም ይካሄዳሉ። ከቀኑ 7 ሰዓት ሃዋሳ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይጫወታሉ። ሃዋሳ ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አራት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። በጨዋታዎቹ ዘጠኝ ግቦችን ሲያስቆጥር ሶስት ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ12 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ተጋጣሚው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በበኩሉ በሊጉ ያከናወናቸውን አምስት ጨዋታዎች አሸንፏል። 13 ግቦችን ሲያስቆጥር የተቆጠረበት አንድ ግብ ብቻ ነው። ቡድኑ በ15 ነጥብ ሊጉን እየመራ ይገኛል። በዘንድሮው የውድድር ዓመት ጥሩ ጅማሮ ያሳዩት ሁለቱ ክለቦች በጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። በሌላኛው መርሃ ግብር ሲዳማ ቡና ከአዲስ አበባ ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሲዳማ ቡና በሊጉ ካደረጋቸው አራት ጨዋታዎች አንድ ጊዜ ሲያሸንፍ ሶስት ጊዜ አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ ሲዳማ ቡና አምስት ግቦችን ሲያስቆጥር ሶስት ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ በስድስት ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው አዲስ አበባ ከተማ በሊጉ ካደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች መካከል አንዱን ሲያሸንፍ አራት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በጨዋታዎቹ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር 11 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በሶስት ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ጨዋታው ሁለቱ ቡድኖች ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ የሚያደርጉት ነው።
በኢትዮጵያ ዋንጫ ቀሪ ስምንት ክለቦች ቀጣዩን ዙር ተቀላቅለዋል
Nov 13, 2025 86
አዲስ አበባ፤ ህዳር 4/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዋንጫ የሁለተኛ ዙር መርሃ ግብር የሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ተደርገዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና አዳማ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። አቡበከር አዳሙ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥሯል። አህመድ ሁሴን ለአዳማ ከተማ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። ባህር ዳር ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አማኑኤል ገብረሚካኤል እና ግርማ ዲሳሳ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ በሬድዋን ሸረፋ ግብ ሃዋሳ ከተማን 1 ለ 0 ረቷል። በተመሳሳይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በመለያ ምት 4 ለ 2 አሸንፏል። ሁለቱ ቡድኖች በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል። በሌሎች ጨዋታዎች አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 2 ለ 1 እና ቢሾፍቱ ከተማ ደሴ ከተማን 1 ለ 0 ሲያሸንፉ ንብ እግር ኳስ ክለብ የካ ክፍለ ከተማን ደብረብርሃን ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማን በመለያ ምት ማሸነፍ ችለዋል። ዛሬ እና ትናንት የተደረጉ ጨዋታዎችን ተከትሎ 16 ክለቦች ለሶስተኛው ዙር አልፈዋል። ኢትዮጵያ መድን፣ ቤንች ማጂ ቡና፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ፣ አርባምንጭ ከተማ፣ ቦዲቲ ከተማ፣ መቀሌ 70 እንደርታ፣ መቻል፣ ነጌሌ አርሲ፣ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ ባህር ዳር ከተማ፣ ደብረብርሃን ከተማ፣ ንብ እግር ኳስ ክለብ፣ ቢሾፍቱ ከተማ፣ ኢትዮጵያ ቡና እና ሲዳማ ቡና 16ቱን የተቀላቀሉ ክለቦች ናቸው። የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ወላይታ ድቻ ከውድድሩ ተሰናብቷል። የኢትዮጵያ ዋንጫ ሶስተኛ ዙር መርሃ ግብር በቀጣይ በሚገለጽ ቀን እና ቦታ ይካሄዳል።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ውጤት ለማምጣት ቁርጠኛ ናት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Nov 14, 2025 80
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 5/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አረጋገጡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የበጋው ደረቅ፣ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ይቀጥላል
Nov 12, 2025 123
አዲስ አበባ፤ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አስር ቀናት በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የበጋው ደረቅ፣ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፥ በሰሜን፣በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ፣ መካከለኛው እና ደቡብ ደጋማ አካባቢዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ እንደሚቀጥል አስታውቋል። በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው የሆኑት የደቡብ፣ደቡብ ምስራቅ እና የደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች ያሳሉ ብሏል። ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ በሰሜን፣ መካከለኛው፣ ምዕራብና ደቡብ ጎንደር ዞኖች፣ባህርዳር ዙሪያ፣ አዊ፣ በምዕራብና ምስራቅ ጎጃም፣ መተከል፣ አሶሳ፣ ካማሺ፣አርሲ፣በባሌ ዞኖች አልፎ አልፎ ሊዘንብ እንደሚችል ኢኒስቲትዩቱ ገልጿል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት በደቡብ ምዕራብ እና ደቡባቢ የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚኖረው መካከለኛ መጠን ያለው ርጥበት ለወቅቱ የግብርና ስራ እንቅስቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው አስታውቋል። የበጋ ርጥበት ተጠቃሚ ተፋሰሶች መጠነኛ የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው የሚጠበቅ ሲሆን የተቀሩት ዝቅተኛ ርጥበት እንደሚኖራቸው ገልጿል። በዚህም አብዛኛው ባሮ አኮቦ፣ መካከለኛው እና ታችኛው ኦሞ ጊቤ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ አባይ እንዲሁም ገናሌ ደዋ መካከለኛ ርጥበት ያገኛሉ፡፡ አብዛኛው አዋሽ፣ዋቤ ሸበሌ፣አፋር ደናክል፣ተከዜ፣ ኦጋዴን ደግሞ ከመጠነኛ ርጥበት እስከ ደረቅ ሁኔታ ይኖራቸዋል ተብሏል።
ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እንድታስተናግድ ተመረጠች
Nov 12, 2025 155
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ ተመርጣለች። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በብራዚል ቤለም እየተካሄደ ይገኛል። ኢትዮጵያ በስብሰባው ላይ ኮፕ 32ትን የማስተናገድ ጥያቄ በይፋ ያቀረበች ሲሆን የአፍሪካ ሀገራት ጉባኤውን እንድታስተናግድ ድጋፍ ሰጥተዋታል። የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀ መንበር ሪቻርድ ሙዩንጊ ቡድኑ የኢትዮጵያን የኮፕ 32 የማስተናገድ ጥያቄ ተቀብሎ ማጽደቁን ለኤኤፍፒ ገልጸዋል። የኮፕ 30 ፕሬዝዳንት የሆነችው ብራዚልም የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያን መምረጣቸውን አረጋግጣለች። የተደራዳሪ ቡድኑ መደበኛ ያልሆነ ውሳኔ በሁሉም የጉባኤው ተሳታፊ ሀገራት መጽደቅ እንደሚጠበቅበት እና ይህም ኮፕ 30 በሚጠናቀቅበት ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ አስተናጋጅነት በድርጅቱ ስር ባሉ አምስት ቀጣናዎች ውስጥ ያሉ ሀገራት በመፈራረቅ የሚያዘጋጁት ነው። ብራዚል የላቲን እና የካሪቢያን ሀገራት ወክላ መመረጧን ተከትሎ ኮፕ 30ን እያካሄደች ትገኛለች። ኮፕ 30 እስከ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን ጉባዔ ለማስተናገድ ከአፍሪካ ሙሉ ድጋፍ አገኘች
Nov 11, 2025 168
አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ እንድታስተናግድ ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝታለች። በብራዚል ቤሌም እየተካሄደ የሚገኘው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መደበኛ ጉባዔውን እያካሄደ ነው። አስቀድሞ በመሪዎች ስብሰባ በጀመረው ጉባዔ ላይ ኢትዮጵያ 32ኛውን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን በአዲስ አበባ ለማዘጋጀት ፍላጎቱም ዝግጁነቱም እንዳላት መግለጿ ይታወሳል። አስቀድሞ በርካታ የጎንዮሽ ውይይቶችን ሲያካሂድ ቆይቶ፥ ቴክኒካዊ ድርድርና ውይይቶችን በሚያስተናግደውና ትላንት በጀመረው ጉባዔ ላይ የኢትዮጵያን ጥያቄ የአፍሪካ ሀገራት መስማማታቸውን ይፋ ማድረጋቸውን የኢቢሲ ዘገባ ያመላክታል። የወቅቱ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር በሆነችው ታንዛኒያ በኩል የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ ተገልጿል። ይህንኑ አስመልክቶ በጉባዔው ንግግር ያደረጉት በብራዚል ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ኢትዮጵያ ጉባዔውን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ አፍሪካውያን በመደገፋቸው ኢትዮጵያ ትልቅ አክብሮት አላት፣ እንደምታሳካው መተማመናቸውም አስደሳች ነው፣ ለዚህም ኢትዮጵያ ታመሰግናለች ማለታቸውንም አስነብቧል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ዳፋን ለመከላከል እየወሰደቻቸው ያሉ ተግባራዊ እርምጃዎች፣ አዲስ አበባ 2ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን ጨምሮ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶችን በስኬት ማስተናገዷ፣ እንዲሁም በሁሉም ረገድ ያላትን ዝግጁነት በመግለጽ ጥያቄዋን ለዘንድሮው ጉባዔ በይፋ ማቅረቧ ይታወሳል። አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ኢትዮጵያ አሁንም የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም ተግባራዊ እርምጃዎችን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። ጉባዔውን ለማስተናገድ ኢትዮጵያ ያቀረበችው ጥያቄ በቀጣይ ሂደቶች ተቀባይነት ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 432
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 572
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል። ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
Oct 31, 2025 475
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው
Oct 24, 2025 738
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡ ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡ በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 40
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 269
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው። በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው። የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው። “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል። በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 341
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 518
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2058
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2310
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3186
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3278
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 1324
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 892
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6730
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5201
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
በጥምር ግብርና ስኬት ያስመዘገቡት አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ
Nov 14, 2025 54
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ - ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ጨዛ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ለዘመናት ባከናወኑት የግብርና ልማት ሥራ ኑሯቸው ከእጅ ወደ አፍ የዘለለ አልነበረም። ዛሬ ላይ ሆነው ያን ዘመንና ያሳለፉትን ዕድሜ ሲያስታውሱ ይቆጫሉ። በኋላ ቀር መንገድ ሲያከናውኑት ከነበረው የግብርና ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ መሆንም፤ ሀብት ማፍራትም ሳይችሉ ቀርተዋል። አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ይባላሉ። ከሰበሰቡት ሰብል ጎተራቸው ሳይጎድል፣ ከእንስሳት እርባታ ስራቸውም ጥገታቸው ሳትነጥፍ ማየት የዘውትር ህልማቸው ነበር። ለም መሬት ይዘው ምርታማ ባለመሆናቸው ሲቸገሩ፣ የሚሰራ ጉልበት ይዘው ማዕዳቸው እየጎደለ የጎልማሳነት ዕድሜ መባቻ ድረስ ችግር ሲፈራረቅባቸው ዓመታትን አሳልፈዋል። ይህ ፍላጎታቸው ሰምሮ፣ ጓሯቸው ለምቶ፣ ቤታቸው ሞልቶና ጥሪት አፍርተው የማየት ውጥናቸው ሳይሳካ ዓመታት ቢቆጠሩም ዛሬ ግን በጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ነገሮች ተቀይረዋል። የዓመታት ምኞታቸውን ማሳካት ጀምረዋል። ከስድስት ዓመታት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ለስኬት እንዲበቁ ከማድረግ ባለፈ በአካባቢያቸው አርአያ የሆኑ አርሶ አደር አድርጓቸዋል። የጥምር ግብርና ስራቸው ለዓመታት ከነበሩበት ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ በማውጣት ለአፍም ለኪስም ሆኗቸዋል። የመንግስት የልማት ትኩረት የሆነው ጥምር ግብርና በውስን መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅንጅት እንዲያለሙ እድል ፍጥሮላቸዋል። በዋናነት በሰብል፣ በእንሰት፣ በፍራፍሬና በእንስሳት እርባታ ላይ አተኩረው እየሰሩ ይገኛሉ። ይህም የአንዱ ክፍተት በሌላው እየተሞለ ውጤታማ ስላደረጋቸው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው። ለቤት ፍጆታ ብቻ ያመርቱ የነበረው የእንሰት ምርትን በማስፋፋት ችግኙንና ተረፈ ምርቱን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጭምር ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያመርቱት ገብስ ለሌሎች አርሶ አደሮች ምሳሌ መሆን ችለዋል። ዝርያቸው የተሻሻሉ ላሞችን ስለሚያረቡም ወተት ከማጀታቸው አይጠፋም። በጓሯቸው የሚያለሙትን አትክልትና ፍራፍሬ ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ፈጥረዋል። አርሶ አደሩ ከንብ ማነብ ሥራቸውም እንዲሁ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው። ከአካባቢው ስነምህዳር ምክንያት ብዙም ያልተለመደውን ቡና በመትከል ለፍሬ አብቅተዋል። የእሳቸውን ፈለግ የተከተሉ ሌሎች አርሶ አደሮችም ቡና ማልማት ጀምረዋል። በእጅ ያለን ሀብት ወደ ውጤት ለመቀየር ተግቶ መስራትና ጽናት ያስፈለጋል ያሉት አርሶ አደር ወልዴ፣ በግብርና ባለሙያዎች የተደረገላቸው ሙያዊ ድጋፍና የተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ለውጤታቸው ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የእርሻ ልማትና የእንስሳት እርባታውን በቅንጅት ማከናወናቸውም እንዲሁ። አርሶ አደር ወልዴ የዓመታት ቁጭታቸው ዛሬ መፍትሄ እያገኘ ነው። የጥምር ግብርና ሥራቸው በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉና ልጆቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እንዲያሳድጉ አስችሏቸዋል። መኖሪያ ቤትን ጨምሮ የተለያየ ሀብት ለማፍራት ምክንያት በመሆኑም ልማቱን አስፋፍቶ ለማከናወን አቅደዋል። አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ጭምር አርአያ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙራዱ ብሩ ናቸው። ቀደም ሲል በገብስ ምርት ላይ ብቻ አተኩረው ይሰሩ የነበረውን የግብርና ሥራ እንዲቀይሩ ምክንያት እንደሆኗቸው ይገልጻሉ። ከአርሶ አደር ወልዴ በወሰዱት ልምድ ወደ ጥምር ግብርና ገብተዋል። በዚህም ድርቅ የመቋቋም አቅም ያለውን እንሰት በማሳቸው በስፋት ማልማት ጀምረዋል። የነበሯቸውን ሀገረሰብ የዳልጋ ከብቶች በተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች በመቀየር የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ተግተው እየሰሩ ነው። ጥምር ግብርና የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ከአርሶ አደር ወልዴ ተምሪያለሁ ይላሉ። ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባለፈ የመሬት ለምነትን ለማስጠበቅም ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ የጀመርነውን ሥራ እናጠናክራለን ሲሉም ነው የገለጹት። የሙህር አክሊል ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ መኑር ጀማል በበኩላቸው "አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ በውስን መሬት ገብስ፣ እንሰት፣ ቡና እና የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በጥምር በማልማት የራሳቸውን ህይወት ከመቀየር ባለፈ ለሌሎች አርሶ አደሮች አርአያ እየሆኑን ነው ብለዋል። አርሶ አደሩ በሽታ መቋቋም የሚችሉና ለመድሃኒትነት የሚፈለጉ የእንሰት ዝርያዎችን በማፍላት ለገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ። ከዚህም ባለፈ በመጥፋት ላይ የነበሩ የእንሰት ዝርያዎችን የመታደግና የአፈር ለምነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውንም ተናግረዋል፡፡ የጥምር ግብርና አሰራር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ በመሆኑ በወረዳው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት። የአርሶ አደር ወልዴ ልምድን በማስፋት የሌሎች አርሶ አደሮችም ጓዳ ሞልቶ እንዲትረፈረፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጥምር ግብርና አርሶ አደሩ ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ጭምር እንዲተርፍ የማድርጉ ሥራ ይጠናከራል ብለዋል። ልማቱ እርስ በእርስ የሚደጋገፉና በአንድ መሬት ላይ የተለያዩ ምርቶችን በማግኘት የተሻለ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚሰራው ሥራ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ በጥቂት መሬት ብዙ ማምረት መቻል ነው። በመሆኑም በተለይ የመሬት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በሥራ ውጤታማ ለመሆን ሁሉም ነገር ምቹና አልጋ በአልጋ መሆን የግድ እንዳልሆነ አርሶ አደሩ ጥሩ ማሳያ ናቸው። ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ዕድል እንዴት ወደሀብትነት መቀየር እችላለሁ ብለው ከሰሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ የእሳቸው የስኬት ጉዞ በቂ ማሳያ ነው። ሰርቶ ለመለወጥም ሆነ ሀብት ለማፍራት ችግሮችን በጽናት ማለፍ እና የሥራ ትጋት ወሳኝ ነውና ተሞክሯቸውን ማስፋት ያስፈልጋል።
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ"
Nov 12, 2025 269
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ" ብርሃኑ ፍቃዱ -ከሰቆጣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልካዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረት ያለው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ማብራራታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ የባህር በሯን ያጣችበትን የ30 ዓመታት ታሪክ ለመቀልበስ ይህን ያህል ዓመት እንደማይወስድ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ ሕጋዊና ተቋማዊ መሰረት የሌለው የሚያስቆጭ ብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል ስለመሆኑም አንስተዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ እና አቶ አድማሱ ደሳለኝ፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር የተወለዱበት ስፍራ፣ የኖሩበት ቀዬ፣ ያሳደጋቸው ማህበረሰብ ... የዘመናት ትዝታና ትውስታቸው እንደሆነ ይገልጻሉ። ይህን የታሪካቸው አካል የሆነውን የባሕር በር ማጣትም የሁል ጊዜ ፀፀትና እንደ ሰውነት ጥላ አብሮዋቸው የሚዞር እውነታ ነው። ከአካባቢው ርቆ ለሚገኝ ሰው ትውስታውን ሲያወራ ለሌላው ተረት ተረት፤ ለራስ ደግሞ የውስጥ ቁስል ማገርሸት ሆኖ ነው የሚሰማው ይላሉ። ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብንና የቀይ ባህር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሸፍጥ ማጣቷ በቀይ ባህር ላይ እየዋኙ፣ ውሃ እየተራጩ፣ በዳርቻው ነፋሻማ ስፍራ እየተዝናኑ... ለኖሩት ለእነ መለሰ እና አድማሱ መቼም የማይረሳ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ለአለም ማሕበረሰብ ጥያቄውን ሲያሳውቁ ተደብቆ ለቆየው ትውስታቸው አዲስ ተስፋ እንደሰጣቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ በአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል ለ12 ዓመታት እንዳገለገሉ በትውስታና ቁጭታቸውን ወደ ኋላ ተመልሰው ያወሳሉ። አሁን በሰቆጣ ከተማ የሚኖሩት አቶ መለሰ ይሄይስ ፤ የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ተደማሪ አቅም ነበር በወቅቱ ይላሉ። ይህን የአሰብ ወደብንና የቀይ ባሕር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሴራ ኢትዮጵያ ስታጣ ይሰሩበት ከነበረው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ስራ አቁመው ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሰቆጣ መምጣታቸውን አውስተዋል። በራሳቸው ላይ ከደረሰባቸው የስራ እና ሃብትና ንብረት ማጣት ፣ እንግልትና ሌሎች ችግሮች በላይ ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተነጠለችበትን ሁኔታ ሲያስቡና ሲያሰላስሉ እንደሚያስቆጫቸው ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን በማጣት የባሕር በር ብቻ ሳይሆን የገቢና ወጭ ንግድን፣ የነዳጅ ማጣሪያ ጭምር ነው ያጣችው ያሉት አቶ መለሰ፤ አሁን ጥያቄው መነሳቱ ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ ገናናነቷ ለመመለስ ያለመ አበረታች ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። መንግስት ያነሳው የባሕር በር ጥያቄም የዘመናት ቁጭታችንን፣ ብስጭታችንን እና ህልማችንን ከተደበቀ ትውስታ፤ ወደ አዲስ ተስፋ የወሰደ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ህጋዊና ታሪካዊ ነው ያሉት አቶ መለሰ ፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝም ለአዲሱ ትውልድ በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። ከ1973 ዓ.ም ጀምረው ለአስር ተከታታይ ዓመታት በአሰብ ወደብ የሲቪል መሃንዲስ ክፍል ሰራተኛ እንደነበሩ ያወሱት አቶ አድማሱ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የባሕር ባር ባለቤት በሆነችባቸው ዘመናት ገናና እና የተከበረች ሀገር ሆና መቆየቷን አንስተዋል። የባሕር በሩ የኢትዮጵያ የገቢና ወጭ ንግድ የሚሳለጥበት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሄን ታላቅ ትሩፋትና ፀጋ ለማስመለስ የተጀመረው እንቅስቃሴ ቁጭትና ትውስታችንን ወደ አዲስ ተስፋ የቀየረ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪካዊ ጠላቶችና ባንዳዎች እኩይ ሴራ የባሕር በር ካጣች ወዲህ ጥያቄውን ማንሳት የማይቻልበት የአፈናው ዘመን አክትሞ በለውጡ መንግስት መነሳቱ አበረታችና ለማስመለስም ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። እኔም ባለኝ አቅም ሁሉ ስለባሕር ባር አስፈላጊነት፣ ጥቅምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ለስኬታማነቱ የድርሻዬ እወጣለሁ ሲሉም ገልጸዋል።