ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል
Mar 6, 2026 76
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዝግጅት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ገለጹ። 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎች ማስመዝገባቸውንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ በተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የመራጮች ምዝገባ ከነገ ጀምሮ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመራጮች ምዝገባ ለአንድ ወር እንደሚካሄድ ገልጸው፤ ምዝገባው በዲጂታል እና በማንዋል መልኩ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል። ከፕሌይ ስቶርና አፕ ስቶር "ምርጫዬ" የተሰኘውን መተግበሪያ አውርደው በስልካቸው መመዝገብ የሚችሉ ዜጎች በራሳቸው መመዝገብ እንደሚችሉም ጠቁመዋል። በአካል ምርጫ ጣቢያዎች የሚመዘገቡ መራጮችን ለማስተናገድም ቦርዱ ለምርጫ አስፈጻሚዎች ታብሌቶችን ማሰራጨቱን አብራርተዋል። ከ3 ጂ በላይ ኢንተርኔት ተደራሽነት ባለባቸው አካበቢዎች የመራጮች ምዝገባው በዲጂታል እንደሚደረግ ጠቁመው፤ ለዚህም ቦርዱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን ማስመዝገባቸውን አክለዋል። ከዚህ ውስጥ 2ሺህ 198 ዕጩዎች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመዘገቡ ሲሆን 8 ሺህ 736 ለክልል ምክር ቤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ እንዳሉት 73 በግል በዕጩነት የቀረቡ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 69ኙ ወንድ 4ቱ ደግሞ ሴት ዕጩዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ቦርዱ ፓርቲዎች የሚወዳደሩበትን ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብንም ፓርቲዎች እንዲፈርሙ መደረጉን ከቅድመ ዝግጅት ስራዎች መካከል መሆኑን አብራርተዋል።
በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት ለመከላከል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በንቃት ሊሰሩ ይገባል
Mar 6, 2026 47
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃትን ለመከላከል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ በንቃት መስራት እንዳለባቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስገነዘበ። 5ኛው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት "ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላምና አካታች ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል መከፈቱ ይታወቃል። የዚሁ መርሃ ግብር አካል የሆነ የ'ኢምፓዚ ፎር ላይፍ ኢንተግሬትድ ዲቨሎፕመንት አሶሴሽን' (ኤሊዳ) (ELIDA) የተዘጋጀ በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት መከላከል ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ሶስት አላማዎችን ያነገበ ነው። እነዚህም ትብብር እና ቅንጅትን ማጠናከር፣ መልካም ተሞክሮዎችን መጋራት እና ለፖሊሲ የሚሆኑ ግብዓቶችን ማሰባሰብ መሆኑን ተናግረዋል። በሴቶች ላይ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት መከላከል ላይ ያደረገው ውይይትም ከዓላማዎቹ አንጻር ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በሀገር ግንባታና በዜጎች ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርገው፣ ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት በንቃትና መስራት እንዳለባቸውም ገልጸዋል። ጠንካራ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕድሎችንና ፈተናዎችን ቀድሞ በመለየት ዘመኑን የዋጀ ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በተለይም በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸውን አንስተዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን ለመከላከል የኅብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግና ጉዳዩን የጋራ አጀንዳ በማድረግ በንቃት መሥራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ተረፈ ዴጌቲ በበኩላቸው፣በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃትን በህግ እና በፖሊሲ ማእቀፎች መከላከል እንደሚገባ ገልጸዋል። ለዚህም የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎም ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። የ'ኢምፓዚ ፎር ላይፍ ኢንተግሬትድ ዲቨሎፕመንት አሶሴሽን' (ኤሊዳ) ዋና ዳይሬክተር ዚነት ይመር ማህበሩ ላለፉት 18 ዓመታት በሴቶች ትምህርት፣ በሰላም ግንባታ እና በኢኮኖሚ ማብቃት ላይ ሰፊ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሰው ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት እየጨመረ መምጣቱ የሴቶችን ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ተሳትፎ እየገደበው መሆኑን ጠቁመዋል። ይህንን ችግር ለመከላከልም የሁሉንም አካላት ትብብር፣ ቅንጅት እና አሳታፊ ምህዳር መፍጠር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል። ማህበሩም ይህንን የጥቃት አይነት በዘላቂነት ለመፍታት በተለያዩ አካባቢዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በስፋት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮጀክት አመራር፣ ትብብር እና የሀብት ማሰባሰብ ቡድን መሪ ሳምሶን ኒሻን ችግሩን ለመከላከል የሴቶች የፖሊሲ ክለሳ ተደርጎ በመጨረሻ ረቂቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ጉዳቱን ለመከላከል ጠንካራ መሰረት እንደሚጥል ገልጸው በስትራቴጂዎችም የተቀመጡ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ከዲጂታል እውቀት አንጻር ውስንነቶች መኖራቸውን አንስተው ተጠቂዎችም ሰፊ የግንዛቤ ክፍተት እንዳለባቸው ገልጸዋል። የሴት መብት ተሟጋች እና በሥርዓተ-ፆታ እኩልነት እንዲሁም በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ የምትሰራው ሰላማዊት ተዘራ ህጎች ቢኖሩም ሰፊ የአፈጻጸም ክፍተት መኖሩን አንስታለች። በቴክኖሎጂ እውቀት ረገድ ሰፊ ክፍተት መኖሩን ገልፀው፣ ችግሩን ለመቅረፍ ተከታታይነት ያላቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መሰጠት እንዳለባቸውም ተናግራለች። በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት ከፍተኛ የስነ ልቦና ጫናን የሚፈጥር መሆኑን የገለጸችው ደግሞ የሥርዓተ-ፆታ እኩልነት እና የማህበራዊ አካታችነት ጥናት ባለሙያ ሀና ለማ ናት። ድርጊቱ ዝቅ ተደርጎ ሳይታይ ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ገልፃለች።
በከተማው ዳሞታ ተራራን ምቹ የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የሚያስችሉ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Mar 6, 2026 48
ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በወላይታ ሶዶ ከተማ የዳሞታ ተራራን ምቹ የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የሚያስችሉ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የከተማው ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መምሪያ በበኩሉ ግንባታውን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ገልጿል። መንግስት ለቱሪዝም ዘርፍ ትኩረት በመስጠት በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ቱሪዝምን ለማሳደግ ግብ ጥሎ እየሰራ መሆኑ የሚታወቅ ነው። የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደርም ከ20 በላይ ነባርና አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን የማልማትና ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡ የከተማው ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሪት ወይንሸት መና ለኢዜአ እንደገለጹት ዳሞታ ተራራን ምቹ የቱሪዝም መዳረሻ ማድረግ የሚያስችሉ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በዳሞታ ተራራ ላይ የተጀመረው የ7ሺህ 187 የደረጃ መወጣጫ ኢኮ ቱሪዝም ሳይት ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ግንባታው በከተሞች አንድ የቱሪዝም መዳረሻ የማልማት ውጥን አካል መሆኑን የገለጹት ሃላፊዋ ሲጠናቀቅም የከተማዋን የቱሪስት ፍሰት በመጨመር ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ያሳድጋል ብለዋል። የከተማው ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መምሪያ የከተማ የተቀናጀ መሠረተ ልማት ሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ አስራት ዳዊት በበኩላቸው፣ የዳሞታ ኢኮ ቱሪዝም ሳይት የደረጃ መወጣጫ ግንባታ በሦስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ እየተገነባ ነው ብለዋል፡፡ የመጀመሪያውን ዙር ግንባታ በ90 ቀናት ለማጠናቀቅ ከተቋራጩ ጋር ውል በመግባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የመወጣጫ ደረጃው በጠቅላላው 5 ነጥብ 3 ኪሎ ሜት ርዝመት ያለው ሲሆን ለቱሪስቶች አገልግሎት የሚሰጡ ሌሎች መዝናኛ ቦታዎችና ተጨማሪ የመንገድ ግንባታን ያካተተ መሆኑም አመልክተዋል። ለመጀመሪያ ዙር ግንባታ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የጠቆሙት አስተባባሪው፣ ለልማቱ በአጠቃላይ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መያዙን ጠቅሰዋል። ግንባታው ሲጠናቀቅ ለቱሪስት ፍሰትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ካለው ጥቅም አንፃር በልዩ ትኩረት እየተመራ መሆኑንም አስታውቀዋል። የሳይቱ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ምሽት ጭምር እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ግንባታውን የሚያከናውነው ሥራ ተቋራጭ አንጆኒዮ ኮንስትራክሽን ሳይት መሀንዲስ መኮንን ተስፋዬ ናቸው፡፡ በግንባታ ሳይቱ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው አቶ ተገኝ ፉርቻካ እና አቶ ኦሎሞ አሰፋ የግንባታው መጀመር የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል፡፡ የቱሪዝም መዳረሻው ሲጠናቀቅ ለአካባቢው ተጨማሪ ዕድልና ተስፋ ይዞ እንደሚመጣ በማመን ሥራቸውን በአግባቡ እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ለመራጭነት የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህርዳርና የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ
Mar 6, 2026 60
ባህር ዳር/ጀረር፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህር ዳር ከተማ እና በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሔደው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ ተአማኒና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ እየሰራ ይገኛል። መራጮች መዝገባም ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጀመር ቦርዱ ያሳወቀ ሲሆን ኢዜአም በባህርዳር ከተማና እና በሶማሌ ክልል ጀረር ዞን ከተሞች ነዋሪዎች መምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ ያላቸውን ዝግጁነት በማስመልከት አነጋግሯል። በባህር ዳር ከተማ ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎቹ መካከል አቶ ሰይፈአርዕድ ሙሏለም እንደገለጹት ዘንድሮ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይመራኛል፤ ያስተዳድረኛል ብለው ያመኑበትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ እየተዘጋጁ ነው። እንደሀገር ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች በንቃት በመሳተፍ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መብታቸውን ማረጋገጣቸውን አስታውሰዋል። ነገ በሚጀምረው የመራጮች ምዝግባም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በምርጫው እለት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ፣ ሀገረ መንግስቱን ለማጽናትና ልማትን ለማፋጠን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ አስፈላጊና ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ነዋሪዋ፣ ህብረተሰቡ በምርጫው ለመሳተፍ በወቅቱ በመመዝገብ የመራጭነት ካርድ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ማረጋገጥና የፈለግነውን ፓርቲ መምረጥ የምንችለው የምርጫ ካርድ በወቅቱ ስንይዝ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ አማረ ጌጡ ናቸው። በተመሳሳይ በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎችም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበጀናል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የዞኑ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ሃይብ ሳላህ በምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ቀኑን እየተጠባበቁ ናቸው። በተለይ የሴቶችን እኩል ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። "በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይሆነኛል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቺያለሁ" ያሉት ደግሞ አቶ አብዱላሂ ዊል መሀሙድ ናቸው። በተለይ ለአገር አድገት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥና ተግቶ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ምርጫቸው መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም በነገው እለት የመራጮች ምዝገባ ካርድ ለመውስድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ከአጠቃላይ የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17 ሺህ ያህሉ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
ረቂቅ አዋጁ የስፖርት እድገትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል
Mar 6, 2026 57
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦የፌዴራል ስፖርት ልማትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ የስፖርት እድገትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ ገለጹ። ቋሚ ኮሚቴው በፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን ለማዳበር የሚያስችል የውይይት መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሂዷል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፤ የስፖርት ዘርፉ የሚመራበት ሁሉን አቀፍ የአሰራር ስርዓትና ህግ አለመኖሩን አንስተዋል። የለውጡ መንግስት ይህን ችግር ለመፍታት የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅቷል ብለዋል። ይህም ጠንካራ፣ ብቁና ጤናማ ትውልድን ለማፍራት፣ ስፖርት ከዜጎች የኑሮ ዘይቤ ጋር የተሳሰረ እንዲሆን አቅም እንዲፈጠር የሚያደርግ ነውም ብለዋል። መንግስት ባለፉት ስምንት ዓመታት የዘርፉን ስብራት ለማከም በከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን ጠቁመው፤ በዚህም ከ17 ሺህ በላይ አነስተኛና መካከለኛ ስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራ በመላ ሀገሪቷ መገንባት መቻሉን ገልጸዋል። ረቂቅ አዋጁ ስፖርት በተጠናከረ ህግና ስርዓት እንዲመራ በማድረግ የዘርፉን እድገት ለማፋጠን አቅም የሚፈጥር ነውም ሲሉ ሚኒስትሯ አክለዋል። በመድረኩ ላይ የተሳተፉ የዘርፉ ተዋናዮች የረቂቅ አዋጁ መዘጋጀት በሀገሪቱ የስፖርት ዘርፉ ውጤታማ እንዳይሆን ማነቆ የሆኑ አሰራሮችን ለመፍታት የሚያስችል እንደሆነ ገልጸው፤ ቢስተካከሉ ያሏቸውን ሀሳቦች አንስተዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱ ለዘርፉ እድገት አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። በረቂቅ አዋጁ ፌዴሬሽኖች ደረጃውን የጠበቀ የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራ ይገነባሉ የሚል ድንጋጌ መኖሩን ጠቁመው፤ ይህ የፌዴሬሽኖችን አቅም ታሳቢ ያደረገ መሆኑን መፈተሽ ያስፈልጋል ብለዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ ፍሬያማ ለማድረግ ከዓለም አቀፍ የስፖርት ህጎች ጋር በተናበበ መልኩ ሊሆን እንደሚገባ ምክረ ሀሳብ ሰጥተዋል። አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ረቂቅ አዋጁ እንደ ሀገር በስፖርት ዘርፉ ላይ የሚፈለገውን ውጤት ለማመጣት ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር በኩል ጉልህ አበርክቶ ይኖረዋል ብሏል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ ቋሚ ኮሚቴው የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ የተደራጀ እንዲሆን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ግብዓት ሲያሰባስብ መቆየቱን ገልጸዋል። የፌዴራል ስፖርት ልማትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ የስፖርት እድገትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ፖለቲካ
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል
Mar 6, 2026 76
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዝግጅት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ገለጹ። 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎች ማስመዝገባቸውንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ በተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የመራጮች ምዝገባ ከነገ ጀምሮ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመራጮች ምዝገባ ለአንድ ወር እንደሚካሄድ ገልጸው፤ ምዝገባው በዲጂታል እና በማንዋል መልኩ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል። ከፕሌይ ስቶርና አፕ ስቶር "ምርጫዬ" የተሰኘውን መተግበሪያ አውርደው በስልካቸው መመዝገብ የሚችሉ ዜጎች በራሳቸው መመዝገብ እንደሚችሉም ጠቁመዋል። በአካል ምርጫ ጣቢያዎች የሚመዘገቡ መራጮችን ለማስተናገድም ቦርዱ ለምርጫ አስፈጻሚዎች ታብሌቶችን ማሰራጨቱን አብራርተዋል። ከ3 ጂ በላይ ኢንተርኔት ተደራሽነት ባለባቸው አካበቢዎች የመራጮች ምዝገባው በዲጂታል እንደሚደረግ ጠቁመው፤ ለዚህም ቦርዱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን ማስመዝገባቸውን አክለዋል። ከዚህ ውስጥ 2ሺህ 198 ዕጩዎች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመዘገቡ ሲሆን 8 ሺህ 736 ለክልል ምክር ቤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ እንዳሉት 73 በግል በዕጩነት የቀረቡ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 69ኙ ወንድ 4ቱ ደግሞ ሴት ዕጩዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ቦርዱ ፓርቲዎች የሚወዳደሩበትን ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብንም ፓርቲዎች እንዲፈርሙ መደረጉን ከቅድመ ዝግጅት ስራዎች መካከል መሆኑን አብራርተዋል።
ለመራጭነት የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህርዳርና የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ
Mar 6, 2026 60
ባህር ዳር/ጀረር፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህር ዳር ከተማ እና በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሔደው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ ተአማኒና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ እየሰራ ይገኛል። መራጮች መዝገባም ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጀመር ቦርዱ ያሳወቀ ሲሆን ኢዜአም በባህርዳር ከተማና እና በሶማሌ ክልል ጀረር ዞን ከተሞች ነዋሪዎች መምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ ያላቸውን ዝግጁነት በማስመልከት አነጋግሯል። በባህር ዳር ከተማ ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎቹ መካከል አቶ ሰይፈአርዕድ ሙሏለም እንደገለጹት ዘንድሮ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይመራኛል፤ ያስተዳድረኛል ብለው ያመኑበትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ እየተዘጋጁ ነው። እንደሀገር ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች በንቃት በመሳተፍ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መብታቸውን ማረጋገጣቸውን አስታውሰዋል። ነገ በሚጀምረው የመራጮች ምዝግባም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በምርጫው እለት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ፣ ሀገረ መንግስቱን ለማጽናትና ልማትን ለማፋጠን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ አስፈላጊና ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ነዋሪዋ፣ ህብረተሰቡ በምርጫው ለመሳተፍ በወቅቱ በመመዝገብ የመራጭነት ካርድ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ማረጋገጥና የፈለግነውን ፓርቲ መምረጥ የምንችለው የምርጫ ካርድ በወቅቱ ስንይዝ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ አማረ ጌጡ ናቸው። በተመሳሳይ በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎችም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበጀናል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የዞኑ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ሃይብ ሳላህ በምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ቀኑን እየተጠባበቁ ናቸው። በተለይ የሴቶችን እኩል ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። "በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይሆነኛል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቺያለሁ" ያሉት ደግሞ አቶ አብዱላሂ ዊል መሀሙድ ናቸው። በተለይ ለአገር አድገት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥና ተግቶ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ምርጫቸው መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም በነገው እለት የመራጮች ምዝገባ ካርድ ለመውስድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ከአጠቃላይ የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17 ሺህ ያህሉ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚያስችለንን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ ተዘጋጅተናል - የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 56
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብታቸውን በመጠቀም ድምጽ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች አስታወቁ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ድምፅ በሚሰጥበት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የአደባባይ መድረክ ነው ብለዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብታቸውን መጠቀም የምርጫ ካርድ በመውሰድ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅት እያደረጉ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። አስራት ወልደሚካኤል እንደገለጹትም፤ ምርጫ ዜጎች የመምረጥና መመረጥ ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን የሚያስከብሩበት የዴሞክራሲ ሥርዓት መገንቢያ መሳሪያ ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ለኢትዮጵያ ዕድገትና ለህዝቦች ተጠቃሚነት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ የምርጫ ምኅዳር መፈጠሩም ጥራት ያለው የምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሥርዓት ወሳኝ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል። በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኅን የሚያቀርቡት የክርክር መድረክም ዜጎች ይበጀኛል ለሚሉት ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት እንደሚያስችል አንስተዋል። ሌላኛዋ አስትያየት ሰጪ ዘነበች አተው በበኩላቸው፤ የመምረጥና መመረጥ መብት በሕገመንግስቱ ለዜጎች የተሰጠ ዴሞክራሲያዊ መብት ነው ብለዋል። ለዚህም በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ሀገርን ወደተሻለ ምዕራፍ ያሻግራል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ምርጫ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን የሚጠቀሙበት የአደባባይ መድረክ ነው ያሉት ደግሞ የሻረግ በሽር ናቸው። በዚህም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ነገ በሚጀመረው የመራጮች ምዝገባ የድምፅ መስጫ የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሬድዮና ቴሌቪዥን የሚያደርጉት የምርጫ ቅስቀሳና የክርክር መድረክ መራጮች የሚሆናቸውን ለመምረጥ ግንዛቤ እየፈጠሩ መሆኑን አንሰተዋል። እንደወጣት ጌታቸው ፀጋዬ ገለፃም፤ በነገው ዕለት በሚጀመረው የመራጮች ምዝገባ ላይ ድምፅ መስጫ ካርድ እንደሚወስድ አስታውቋል። በምርጫ ወቅት የአንድ ሰው ድምፅ ትልቅ ዋጋ አለው ያለው ወጣት ጌታቸው፤ ለዚህም ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለመጠቀም ድምፅ መስጫ ካርድ እንደሚወስድ ገልጿል።
ሴቶች በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ለዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል
Mar 6, 2026 59
ደሴ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡-ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሑመድ አስገነዘቡ። የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን "50 ዓመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሀሳብ በወሎ ዩኒቨርሲቲ በፓናል ውይይት ተከብሯል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሑመድ በወቅቱ አንደገለጹት፣ የሴቶችን ሁለተናዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ በማሳደግ የኢትዮጵያን ሁለተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው። ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማትም ሚናቸውን የበለጠ እንዲወጡ አሳስበዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶችን የመሪነት እና የውሳኔ ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በተደረገው ጥረት አበረታች ውጤት መመዝገቡን የተናገሩት ምክትል አፈ ጉባኤዋ፣ በምርጫው በመምረጥና በመመረጥ ፖለቲካዊ ተሳትፏቸውን ሊያጎለብቱ ይገባል ብለዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ በበኩላቸው፣ በክልሉ የሴቶችን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ ለማሳደግ እየተደረገ ያለው ጥረት ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በየደረጃው እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ሴቶች ይበጀናል ያሉትን በመምረጥ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ አስገንዝበዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ነጻ እንዲሆን በየደረጃው የየድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። በወሎ ዩኒቨርሲቲ የሶሾሎጂ መመህርና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር ፋጡማ አብዱ በበኩላቸው፣ የሴቶች ሁለተናዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ እንዲያድግ አንድነታችንን ጠብቀን እንሰራለን ብለዋል። በውይይቱ የፌዴራል፣ የክልል፣ የወሎ የኒቨርሲቲና የደሴ ከተማ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል - የመዲናዋ ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 107
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊና ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ለዚህም የመራጮች ምዝገባ ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች በይፋ ይጀመራል። ኢዜአ በአዲስ ከተማና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች ባደረገው የመስክ ቅኝት ለመራጮች ምዝገባ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች ወደ ተለያዩ ወረዳዎችና ምርጫ ጣቢያዎች እየተጓጓዙ መሆኑን ተመልክቷል። የመዲናዋ ነዋሪዎች ምርጫው ለአገር ዕድገትና ለዜጎች ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና ያለው በመሆኑ ቀድሞ ለመመዝገብና ለመምረጥ ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከልም አቶ ሞላ ስለሺ እንደገለጹት፤ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ተዘጋጅተዋል፡፡ በዚህም በመጪው ግንቦት ወር በሚካሔደው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውንም ነው የገለጹት፡፡ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ብርሃኑ ጣሰው በበኩላቸው የሀገርን ልማትና ዕድገት ይበጃል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ግንባር ቀደም ተመዝጋቢና መራጭ እንደሚሆኑ ገልጸዋል። በተለይም በመገናኛ ብዙኃን የሚደረጉ ክርክሮች የተሻለ አማራጭ ሐሳብ ያላቸውን ፓርቲዎች ለመለየት እንደሚረዷቸው ጠቁመዋል። ወጣት ኢሳ ሰሂድ ምርጫ ለአንድ አገር መሠረት፣ ለሕዝቦች አንድነትና የጋራ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን በመጥቀስ፤ የተሻለ ነገን ይፈጥራል የሚሉትን ለመምረጥ በንቃት እንደሚሳተፍ አስታውቋል። በነገው ዕለት በሚጀመረው ምዝገባ የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መጓጓቷን የገለጸችው ወጣት ራሔል ገዛህኝ በበኩሏ፤ ምርጫ ይበጀኛል ለምለው ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት የሚያስችለኝ ሕግ መንግስታዊ መብት በመሆኑ ይህንን ዕድል ለመጠቀም ዝግጁ ነኝ ብላለች፡፡ አስተያየት ሰጪዎቹ ምርጫው ለአገር ዕድገትና ለዜጎች ተጠቃሚነት ያለውን የጎላ ሚና በመረዳት ነገ በሚጀምረው የመራጮች ምዝገባ ላይ በንቃት ለመሳተፍ በከፍተኛ ተነሳሽነት ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ በመሆኑ ዜጎች የነቃ ተሣትፎ እንዲያደርጉ የበኩላችንን እንወጣለን - የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች
Mar 6, 2026 91
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ በመሆኑ ዜጎች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የነቃ ተሣትፎ እንዲያደርጉ የበኩላቸውን እንደሚወጡ የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ለዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የዕጩዎች ምዝገባ የተከናወነ ሲሆን የመራጮች ምዝገባም ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 በሁሉም የምርጫ ጣቢዎች ይጀመራል፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኃላፊዎች ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊነት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነው ብለዋል። ምርጫ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መሰረት በመሆኑ ዜጎች ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ነገ በሚጀመረው የመራጮች ምዝገባ የምርጫ ካርዳቸውን መውሰድ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ነዋል አቡበከር፤ ከ180 በላይ ድርጅቶችን አቅፈው እንደሚንቀሳቀሱ ጠቅሰው፤ የህዝቡን የፖለቲካ ተሳትፎ ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ መራጮች በቂ እውቀት ኖሯቸው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዲሳተፉ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ምርጫን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የምርጫውን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ከ5 ሺህ በላይ ታዛቢዎችን ማዘጋጀታቸውን አክለው ታዛቢዎቹ በመላው አገሪቱ ተሰማርተው የምርጫውን ሂደት በቅርበት እንዲከታተሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ሁሉም ድርጅቶች ዜጎች ነገ በሚጀምረው የመራጮች ምዝገባ ላይ በመሳተፍ የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ድርጅት ኅብረት ዳይሬክተር አቶ መሱድ ገበየሁ እንደገለጹት፤ ምርጫ ዜጎች ትልቅ የፖለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉበትና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱ የሚረጋገጥበት ሂደት ነው። ኅብረቱ ሂደቱ ዴሞክራሲያዊ፣ ግልጽና ተዓማኒ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የምርጫ ሂደቱን ለመታዘብ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቃቸውንም ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የአካል ጉዳተኞች የድርጊት መረብ ስራ አስኪያጅ አቶ አለሙ ኃይሌ በበኩላቸው ጥምረቱ በተለይ የአካል ጉዳተኞች በመራጭነትና በተመራጭነት ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የአካል ጉዳተኞች በሁሉም ዘርፍ ያላቸው ተሳትፎ እንዲጎለብት በአገር አቀፍ ደረጃ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ዝግጁ ነን - የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 94
መቱ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ዘንድሮ በሚካሄደው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን በኦሮሚያ ክልል የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ። ካርድ ወስደን በመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል -የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም የሚካሔደው ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ እየሰራ ይገኛል። ከዝግጅቶቹ መካከል ከነገ የካቲት 28/2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሔደው የመራጮች ምዝገባ ተጠቃሽ ነው። ቦርዱ በአጠቃላይ ከሚኖሩት የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17ሺህ ያህሉ የዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቦር ዞን የሁሩሙ ወረዳ ነዋሪዋ ህዝባለም ደገፉ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ መብቴን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ እየተጠባበኩ ነው ብለዋል። የመቱ ወረዳ ነዋሪዋ ዝማርጉ ጀማል እና ናሐዊ ደፋር በበኩላቸው፤ በመራጭነት ተመዝግበው መብታቸውን ለመጠቀም እንዲችሉ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ምርጫ ለሀገረ መግሥት ግንባታ ወሳኝ ምእራፍ በመሆኑ የዜግነት ግዴታዬን በኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ ነኝ የሚለው ደግሞ የመቱ ከተማ ነዋሪው ወጣት በፈቃዱ እንዳለ ነው። ወጣት ፌዴሳ ታረቀኝ እና ግርማ ፍሪሳ በበኩላቸው፤ ጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እንደ ወጣት የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል። በሀገረ መንግስት ግንባታ ውስጥ ሴቶችና ወጣቶች የሚኖራቸው ሚና የላቀ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ በመውሰድ የሚወክለንን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። በተለይም በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚውና በማህበራዊ ዘርፎች ዘላቂ ተጠቃሚነታችን የሚያረጋግጥልን ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት የመራጮች ምዝገባ እስኪጀመር እየጠበቅን ነው ብለዋል።
የጥፋት ቡድኑን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን - የትግራይ ተወላጆች
Mar 6, 2026 154
ሐረር/አሶሳ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለጥፋት የቆመውን የህወሓት ቡድን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በሐረር እና በአሶሳ ከተሞች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ። የትግራይ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሰሞኑን በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ እንደሆነ ጠቁመው የሰላም እና ልማት ፍላጎቱ ትልቅ መሆኑን ገልጸዋል። በሁሉም ክልሎች እየመጣ ያለው ልማትና ሰላም የትግራይ ህዝብም ይገባዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአረጀ አስተሳሰብ ለዳግም ጦርነትና ውድመት የሚጥረው የሕወሓት ቡድን ተው ሊባል ይገባል ማለታቸው ይታወሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ በሐረር እና በአሶሳ ከተሞች ኢዜአ ያነጋገራቸው የትግራይ ተወላጆች፤ የህወሓት ቡድን ከጥፋትና የጦርነት እቅድ በስተቀር ለህዝብ ሰላምና ልማት መስራት የማይፈልግ ስብስብ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቡድኑን እኩይ ዓላማ እና የህዝቡን የሰላምና የልማት ፍላጎት በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ ተክክለኛ እና ወቅታዊ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ በመደገፍ ለጥፋት የቆመውን ቡድን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን ነው ያሉት። በሐረር ከተማ የሚኖሩት ወይዘሮ ጊዮርጊስ ሃጎስ፤ የጥፋት ቡድኑ መቼም ቢሆን ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ልማት ሰርቶ የማያውቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት ከማይሻው የሻዕቢያ መንግስት ጋር ግንባር በመፍጠር አካባቢውን የጦርነት ቀጣና ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸው ይህንን እኩይ ዓላማ በፅኑ እንታገለዋለን ብለዋል። የአሶሳ ከተማ ነዋሪው ጎይቶም በየነ፤ የህወሓት የጥፋት ቡድን እሳቤ ጊዜው ያለፈበትና ለማንም የማይጠቅም መሆኑንና የትግራይ ህዝብ አሁን ላይ እንደሌሎች ክልሎች በአዲስ እሳቤና በአዲስ ትውልድ መመራትን አጥብቆ ይሻል ብለዋል። በመሆኑም የህወሓትን ቡድን ጊዜው ያለፈበት አስተሳሰብ በጋራ በመታገል ለክልሉ ሰላም፣ ልማትና ተጠቃሚነት በተባበረ አቅም እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። በሐረር ከተማ የሚኖረው ሼኖክ ሊላይ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ያስተላለፉት መልእክት ለሀገር ሰላምና ልማት የሚጠቅም በመሆኑ ሁላችንም የምንደግፈው ነው ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደ ሌሎች ክልሎች ሁሉ ለትግራይ ክልል ህዝብ ሰላም፣ ልማትና እድገት ያስፈልገዋል ማለታቸው ተገቢ መሆኑን አንስቶ ለዚህም በተለይም የክልሉ ተወላጆች የበኩላችንን እንወጣለን ሲል ተናግሯል። ሌላኛው በአሶሳ ከተማ የሚኖረው ወጣት ክብሮም ገብረመድህን፤ በኢትዮጵያ ከመጣው ለውጥና ሁለንተናዊ የልማት እቅዶች ተጠቃሚ ለመሆን የትግራይ ህዝብ አጥብቆ ይሻል ሲል ገልጿል። ይህንን እውን ለማድረግ ደግሞ ለግጭትና ጦርነት እየሰራ የሚገኘውን የህወሓት የጥፋት ስብስብን በጋራ መታገል ሲቻል ብቻ መሆኑን ገልፆ ለዚህም በተለይ ወጣቶች አደራችንን ለመወጣት እንሰራለን ብሏል። በሐረር ከተማ ያገኘናቸው ወጣት ሳሙኤል መለስ እና ወጣት ፍሬህይወት ብርሃነ፤ የትግራይ ወጣቶች አሁን ላይ የህወሓትን የጦርነት ነጋሪት ሸሽተው እየተሰደዱ መሆኑን አንስተው ነገር ግን ስደት መፍትሄ የማያመጣ በመሆኑ ለትግራይ ህዝብ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና ለውጥ እንዲመጣ በትብብር እንሰራለን ብለዋል።
ፖለቲካ
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ ዝግጅት ተጠናቋል
Mar 6, 2026 76
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዝግጅት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ገለጹ። 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎች ማስመዝገባቸውንም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ በተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የመራጮች ምዝገባ ከነገ ጀምሮ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመራጮች ምዝገባ ለአንድ ወር እንደሚካሄድ ገልጸው፤ ምዝገባው በዲጂታል እና በማንዋል መልኩ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል። ከፕሌይ ስቶርና አፕ ስቶር "ምርጫዬ" የተሰኘውን መተግበሪያ አውርደው በስልካቸው መመዝገብ የሚችሉ ዜጎች በራሳቸው መመዝገብ እንደሚችሉም ጠቁመዋል። በአካል ምርጫ ጣቢያዎች የሚመዘገቡ መራጮችን ለማስተናገድም ቦርዱ ለምርጫ አስፈጻሚዎች ታብሌቶችን ማሰራጨቱን አብራርተዋል። ከ3 ጂ በላይ ኢንተርኔት ተደራሽነት ባለባቸው አካበቢዎች የመራጮች ምዝገባው በዲጂታል እንደሚደረግ ጠቁመው፤ ለዚህም ቦርዱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን ማስመዝገባቸውን አክለዋል። ከዚህ ውስጥ 2ሺህ 198 ዕጩዎች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመዘገቡ ሲሆን 8 ሺህ 736 ለክልል ምክር ቤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ እንዳሉት 73 በግል በዕጩነት የቀረቡ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 69ኙ ወንድ 4ቱ ደግሞ ሴት ዕጩዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ቦርዱ ፓርቲዎች የሚወዳደሩበትን ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብንም ፓርቲዎች እንዲፈርሙ መደረጉን ከቅድመ ዝግጅት ስራዎች መካከል መሆኑን አብራርተዋል።
ለመራጭነት የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህርዳርና የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ
Mar 6, 2026 60
ባህር ዳር/ጀረር፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ የሚፈልጉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የባህር ዳር ከተማ እና በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎች ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሔደው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ ተአማኒና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ እየሰራ ይገኛል። መራጮች መዝገባም ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጀመር ቦርዱ ያሳወቀ ሲሆን ኢዜአም በባህርዳር ከተማና እና በሶማሌ ክልል ጀረር ዞን ከተሞች ነዋሪዎች መምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ ያላቸውን ዝግጁነት በማስመልከት አነጋግሯል። በባህር ዳር ከተማ ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎቹ መካከል አቶ ሰይፈአርዕድ ሙሏለም እንደገለጹት ዘንድሮ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይመራኛል፤ ያስተዳድረኛል ብለው ያመኑበትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ከወዲሁ እየተዘጋጁ ነው። እንደሀገር ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች በንቃት በመሳተፍ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መብታቸውን ማረጋገጣቸውን አስታውሰዋል። ነገ በሚጀምረው የመራጮች ምዝግባም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በምርጫው እለት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ፣ ሀገረ መንግስቱን ለማጽናትና ልማትን ለማፋጠን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ አስፈላጊና ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ነዋሪዋ፣ ህብረተሰቡ በምርጫው ለመሳተፍ በወቅቱ በመመዝገብ የመራጭነት ካርድ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ማረጋገጥና የፈለግነውን ፓርቲ መምረጥ የምንችለው የምርጫ ካርድ በወቅቱ ስንይዝ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ አማረ ጌጡ ናቸው። በተመሳሳይ በሶማሌ ክልል የጀረር ዞን ነዋሪዎችም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይበጀናል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የዞኑ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ሃይብ ሳላህ በምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ቀኑን እየተጠባበቁ ናቸው። በተለይ የሴቶችን እኩል ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። "በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ይሆነኛል የምለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅቺያለሁ" ያሉት ደግሞ አቶ አብዱላሂ ዊል መሀሙድ ናቸው። በተለይ ለአገር አድገት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥና ተግቶ የሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ምርጫቸው መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀም በነገው እለት የመራጮች ምዝገባ ካርድ ለመውስድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ከአጠቃላይ የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17 ሺህ ያህሉ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚያስችለንን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ ተዘጋጅተናል - የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 56
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብታቸውን በመጠቀም ድምጽ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች አስታወቁ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ድምፅ በሚሰጥበት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርጉበት የአደባባይ መድረክ ነው ብለዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብታቸውን መጠቀም የምርጫ ካርድ በመውሰድ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅት እያደረጉ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። አስራት ወልደሚካኤል እንደገለጹትም፤ ምርጫ ዜጎች የመምረጥና መመረጥ ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን የሚያስከብሩበት የዴሞክራሲ ሥርዓት መገንቢያ መሳሪያ ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ለኢትዮጵያ ዕድገትና ለህዝቦች ተጠቃሚነት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ የምርጫ ምኅዳር መፈጠሩም ጥራት ያለው የምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሥርዓት ወሳኝ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል። በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኅን የሚያቀርቡት የክርክር መድረክም ዜጎች ይበጀኛል ለሚሉት ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት እንደሚያስችል አንስተዋል። ሌላኛዋ አስትያየት ሰጪ ዘነበች አተው በበኩላቸው፤ የመምረጥና መመረጥ መብት በሕገመንግስቱ ለዜጎች የተሰጠ ዴሞክራሲያዊ መብት ነው ብለዋል። ለዚህም በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ድምፅ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በመውሰድ ሀገርን ወደተሻለ ምዕራፍ ያሻግራል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ምርጫ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን የሚጠቀሙበት የአደባባይ መድረክ ነው ያሉት ደግሞ የሻረግ በሽር ናቸው። በዚህም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ነገ በሚጀመረው የመራጮች ምዝገባ የድምፅ መስጫ የምርጫ ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሬድዮና ቴሌቪዥን የሚያደርጉት የምርጫ ቅስቀሳና የክርክር መድረክ መራጮች የሚሆናቸውን ለመምረጥ ግንዛቤ እየፈጠሩ መሆኑን አንሰተዋል። እንደወጣት ጌታቸው ፀጋዬ ገለፃም፤ በነገው ዕለት በሚጀመረው የመራጮች ምዝገባ ላይ ድምፅ መስጫ ካርድ እንደሚወስድ አስታውቋል። በምርጫ ወቅት የአንድ ሰው ድምፅ ትልቅ ዋጋ አለው ያለው ወጣት ጌታቸው፤ ለዚህም ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለመጠቀም ድምፅ መስጫ ካርድ እንደሚወስድ ገልጿል።
ሴቶች በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ለዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል
Mar 6, 2026 59
ደሴ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡-ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሑመድ አስገነዘቡ። የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን "50 ዓመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሀሳብ በወሎ ዩኒቨርሲቲ በፓናል ውይይት ተከብሯል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሑመድ በወቅቱ አንደገለጹት፣ የሴቶችን ሁለተናዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ በማሳደግ የኢትዮጵያን ሁለተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው። ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ልማትም ሚናቸውን የበለጠ እንዲወጡ አሳስበዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶችን የመሪነት እና የውሳኔ ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በተደረገው ጥረት አበረታች ውጤት መመዝገቡን የተናገሩት ምክትል አፈ ጉባኤዋ፣ በምርጫው በመምረጥና በመመረጥ ፖለቲካዊ ተሳትፏቸውን ሊያጎለብቱ ይገባል ብለዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ በበኩላቸው፣ በክልሉ የሴቶችን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ ለማሳደግ እየተደረገ ያለው ጥረት ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በየደረጃው እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ሴቶች ይበጀናል ያሉትን በመምረጥ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ አስገንዝበዋል። ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ነጻ እንዲሆን በየደረጃው የየድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። በወሎ ዩኒቨርሲቲ የሶሾሎጂ መመህርና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር ፋጡማ አብዱ በበኩላቸው፣ የሴቶች ሁለተናዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ እንዲያድግ አንድነታችንን ጠብቀን እንሰራለን ብለዋል። በውይይቱ የፌዴራል፣ የክልል፣ የወሎ የኒቨርሲቲና የደሴ ከተማ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል - የመዲናዋ ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 107
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጭነት ካርድ በመውሰድ ዴሞክራሲያዊና ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ለዚህም የመራጮች ምዝገባ ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች በይፋ ይጀመራል። ኢዜአ በአዲስ ከተማና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች ባደረገው የመስክ ቅኝት ለመራጮች ምዝገባ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች ወደ ተለያዩ ወረዳዎችና ምርጫ ጣቢያዎች እየተጓጓዙ መሆኑን ተመልክቷል። የመዲናዋ ነዋሪዎች ምርጫው ለአገር ዕድገትና ለዜጎች ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና ያለው በመሆኑ ቀድሞ ለመመዝገብና ለመምረጥ ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከልም አቶ ሞላ ስለሺ እንደገለጹት፤ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ ተዘጋጅተዋል፡፡ በዚህም በመጪው ግንቦት ወር በሚካሔደው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም መዘጋጀታቸውንም ነው የገለጹት፡፡ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ብርሃኑ ጣሰው በበኩላቸው የሀገርን ልማትና ዕድገት ይበጃል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ግንባር ቀደም ተመዝጋቢና መራጭ እንደሚሆኑ ገልጸዋል። በተለይም በመገናኛ ብዙኃን የሚደረጉ ክርክሮች የተሻለ አማራጭ ሐሳብ ያላቸውን ፓርቲዎች ለመለየት እንደሚረዷቸው ጠቁመዋል። ወጣት ኢሳ ሰሂድ ምርጫ ለአንድ አገር መሠረት፣ ለሕዝቦች አንድነትና የጋራ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን በመጥቀስ፤ የተሻለ ነገን ይፈጥራል የሚሉትን ለመምረጥ በንቃት እንደሚሳተፍ አስታውቋል። በነገው ዕለት በሚጀመረው ምዝገባ የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መጓጓቷን የገለጸችው ወጣት ራሔል ገዛህኝ በበኩሏ፤ ምርጫ ይበጀኛል ለምለው ፓርቲ ድምፅ ለመስጠት የሚያስችለኝ ሕግ መንግስታዊ መብት በመሆኑ ይህንን ዕድል ለመጠቀም ዝግጁ ነኝ ብላለች፡፡ አስተያየት ሰጪዎቹ ምርጫው ለአገር ዕድገትና ለዜጎች ተጠቃሚነት ያለውን የጎላ ሚና በመረዳት ነገ በሚጀምረው የመራጮች ምዝገባ ላይ በንቃት ለመሳተፍ በከፍተኛ ተነሳሽነት ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ በመሆኑ ዜጎች የነቃ ተሣትፎ እንዲያደርጉ የበኩላችንን እንወጣለን - የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች
Mar 6, 2026 91
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ በመሆኑ ዜጎች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የነቃ ተሣትፎ እንዲያደርጉ የበኩላቸውን እንደሚወጡ የተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ለዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የዕጩዎች ምዝገባ የተከናወነ ሲሆን የመራጮች ምዝገባም ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 በሁሉም የምርጫ ጣቢዎች ይጀመራል፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኃላፊዎች ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊነት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነው ብለዋል። ምርጫ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መሰረት በመሆኑ ዜጎች ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ነገ በሚጀመረው የመራጮች ምዝገባ የምርጫ ካርዳቸውን መውሰድ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ነዋል አቡበከር፤ ከ180 በላይ ድርጅቶችን አቅፈው እንደሚንቀሳቀሱ ጠቅሰው፤ የህዝቡን የፖለቲካ ተሳትፎ ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ መራጮች በቂ እውቀት ኖሯቸው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዲሳተፉ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ምርጫን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የምርጫውን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ከ5 ሺህ በላይ ታዛቢዎችን ማዘጋጀታቸውን አክለው ታዛቢዎቹ በመላው አገሪቱ ተሰማርተው የምርጫውን ሂደት በቅርበት እንዲከታተሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ሁሉም ድርጅቶች ዜጎች ነገ በሚጀምረው የመራጮች ምዝገባ ላይ በመሳተፍ የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ድርጅት ኅብረት ዳይሬክተር አቶ መሱድ ገበየሁ እንደገለጹት፤ ምርጫ ዜጎች ትልቅ የፖለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉበትና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱ የሚረጋገጥበት ሂደት ነው። ኅብረቱ ሂደቱ ዴሞክራሲያዊ፣ ግልጽና ተዓማኒ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የምርጫ ሂደቱን ለመታዘብ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቃቸውንም ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የአካል ጉዳተኞች የድርጊት መረብ ስራ አስኪያጅ አቶ አለሙ ኃይሌ በበኩላቸው ጥምረቱ በተለይ የአካል ጉዳተኞች በመራጭነትና በተመራጭነት ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የአካል ጉዳተኞች በሁሉም ዘርፍ ያላቸው ተሳትፎ እንዲጎለብት በአገር አቀፍ ደረጃ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ዝግጁ ነን - የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች
Mar 6, 2026 94
መቱ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ዘንድሮ በሚካሄደው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ የሚያስችላቸውን የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን በኦሮሚያ ክልል የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ። ካርድ ወስደን በመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለመጠቀም ተዘጋጅተናል -የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም የሚካሔደው ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ እየሰራ ይገኛል። ከዝግጅቶቹ መካከል ከነገ የካቲት 28/2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሔደው የመራጮች ምዝገባ ተጠቃሽ ነው። ቦርዱ በአጠቃላይ ከሚኖሩት የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ17ሺህ ያህሉ የዲጂታል የመራጮች ምዝገባን ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቦር ዞን የሁሩሙ ወረዳ ነዋሪዋ ህዝባለም ደገፉ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ መብቴን ለመጠቀም የመራጭነት ካርድ ለመውሰድ እየተጠባበኩ ነው ብለዋል። የመቱ ወረዳ ነዋሪዋ ዝማርጉ ጀማል እና ናሐዊ ደፋር በበኩላቸው፤ በመራጭነት ተመዝግበው መብታቸውን ለመጠቀም እንዲችሉ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ምርጫ ለሀገረ መግሥት ግንባታ ወሳኝ ምእራፍ በመሆኑ የዜግነት ግዴታዬን በኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ ነኝ የሚለው ደግሞ የመቱ ከተማ ነዋሪው ወጣት በፈቃዱ እንዳለ ነው። ወጣት ፌዴሳ ታረቀኝ እና ግርማ ፍሪሳ በበኩላቸው፤ ጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እንደ ወጣት የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል። በሀገረ መንግስት ግንባታ ውስጥ ሴቶችና ወጣቶች የሚኖራቸው ሚና የላቀ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን በመገንዘብ የምርጫ ካርድ በመውሰድ የሚወክለንን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። በተለይም በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚውና በማህበራዊ ዘርፎች ዘላቂ ተጠቃሚነታችን የሚያረጋግጥልን ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት የመራጮች ምዝገባ እስኪጀመር እየጠበቅን ነው ብለዋል።
የጥፋት ቡድኑን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን - የትግራይ ተወላጆች
Mar 6, 2026 154
ሐረር/አሶሳ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ ለጥፋት የቆመውን የህወሓት ቡድን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ በሐረር እና በአሶሳ ከተሞች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ። የትግራይ ህዝብ የሰላምና የልማት ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የህወሃትን የጥፋት ቡድን በጽኑ ሊታገል ይገባል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሰሞኑን በትግርኛ ቋንቋ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ የትግራይ ህዝብ ለሰላም እና ልማት የታገለ እንደሆነ ጠቁመው የሰላም እና ልማት ፍላጎቱ ትልቅ መሆኑን ገልጸዋል። በሁሉም ክልሎች እየመጣ ያለው ልማትና ሰላም የትግራይ ህዝብም ይገባዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአረጀ አስተሳሰብ ለዳግም ጦርነትና ውድመት የሚጥረው የሕወሓት ቡድን ተው ሊባል ይገባል ማለታቸው ይታወሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ በሐረር እና በአሶሳ ከተሞች ኢዜአ ያነጋገራቸው የትግራይ ተወላጆች፤ የህወሓት ቡድን ከጥፋትና የጦርነት እቅድ በስተቀር ለህዝብ ሰላምና ልማት መስራት የማይፈልግ ስብስብ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቡድኑን እኩይ ዓላማ እና የህዝቡን የሰላምና የልማት ፍላጎት በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ ተክክለኛ እና ወቅታዊ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ በመደገፍ ለጥፋት የቆመውን ቡድን በመታገል ለትግራይ ሰላምና ልማት የበኩላችንን እንወጣለን ነው ያሉት። በሐረር ከተማ የሚኖሩት ወይዘሮ ጊዮርጊስ ሃጎስ፤ የጥፋት ቡድኑ መቼም ቢሆን ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ልማት ሰርቶ የማያውቅ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት ከማይሻው የሻዕቢያ መንግስት ጋር ግንባር በመፍጠር አካባቢውን የጦርነት ቀጣና ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸው ይህንን እኩይ ዓላማ በፅኑ እንታገለዋለን ብለዋል። የአሶሳ ከተማ ነዋሪው ጎይቶም በየነ፤ የህወሓት የጥፋት ቡድን እሳቤ ጊዜው ያለፈበትና ለማንም የማይጠቅም መሆኑንና የትግራይ ህዝብ አሁን ላይ እንደሌሎች ክልሎች በአዲስ እሳቤና በአዲስ ትውልድ መመራትን አጥብቆ ይሻል ብለዋል። በመሆኑም የህወሓትን ቡድን ጊዜው ያለፈበት አስተሳሰብ በጋራ በመታገል ለክልሉ ሰላም፣ ልማትና ተጠቃሚነት በተባበረ አቅም እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። በሐረር ከተማ የሚኖረው ሼኖክ ሊላይ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ያስተላለፉት መልእክት ለሀገር ሰላምና ልማት የሚጠቅም በመሆኑ ሁላችንም የምንደግፈው ነው ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደ ሌሎች ክልሎች ሁሉ ለትግራይ ክልል ህዝብ ሰላም፣ ልማትና እድገት ያስፈልገዋል ማለታቸው ተገቢ መሆኑን አንስቶ ለዚህም በተለይም የክልሉ ተወላጆች የበኩላችንን እንወጣለን ሲል ተናግሯል። ሌላኛው በአሶሳ ከተማ የሚኖረው ወጣት ክብሮም ገብረመድህን፤ በኢትዮጵያ ከመጣው ለውጥና ሁለንተናዊ የልማት እቅዶች ተጠቃሚ ለመሆን የትግራይ ህዝብ አጥብቆ ይሻል ሲል ገልጿል። ይህንን እውን ለማድረግ ደግሞ ለግጭትና ጦርነት እየሰራ የሚገኘውን የህወሓት የጥፋት ስብስብን በጋራ መታገል ሲቻል ብቻ መሆኑን ገልፆ ለዚህም በተለይ ወጣቶች አደራችንን ለመወጣት እንሰራለን ብሏል። በሐረር ከተማ ያገኘናቸው ወጣት ሳሙኤል መለስ እና ወጣት ፍሬህይወት ብርሃነ፤ የትግራይ ወጣቶች አሁን ላይ የህወሓትን የጦርነት ነጋሪት ሸሽተው እየተሰደዱ መሆኑን አንስተው ነገር ግን ስደት መፍትሄ የማያመጣ በመሆኑ ለትግራይ ህዝብ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና ለውጥ እንዲመጣ በትብብር እንሰራለን ብለዋል።
ማህበራዊ
በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት ለመከላከል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በንቃት ሊሰሩ ይገባል
Mar 6, 2026 47
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃትን ለመከላከል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ በንቃት መስራት እንዳለባቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስገነዘበ። 5ኛው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት "ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላምና አካታች ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል መከፈቱ ይታወቃል። የዚሁ መርሃ ግብር አካል የሆነ የ'ኢምፓዚ ፎር ላይፍ ኢንተግሬትድ ዲቨሎፕመንት አሶሴሽን' (ኤሊዳ) (ELIDA) የተዘጋጀ በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት መከላከል ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፋሲካው ሞላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ሶስት አላማዎችን ያነገበ ነው። እነዚህም ትብብር እና ቅንጅትን ማጠናከር፣ መልካም ተሞክሮዎችን መጋራት እና ለፖሊሲ የሚሆኑ ግብዓቶችን ማሰባሰብ መሆኑን ተናግረዋል። በሴቶች ላይ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት መከላከል ላይ ያደረገው ውይይትም ከዓላማዎቹ አንጻር ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በሀገር ግንባታና በዜጎች ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርገው፣ ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት በንቃትና መስራት እንዳለባቸውም ገልጸዋል። ጠንካራ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕድሎችንና ፈተናዎችን ቀድሞ በመለየት ዘመኑን የዋጀ ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በተለይም በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸውን አንስተዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን ለመከላከል የኅብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግና ጉዳዩን የጋራ አጀንዳ በማድረግ በንቃት መሥራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ተረፈ ዴጌቲ በበኩላቸው፣በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃትን በህግ እና በፖሊሲ ማእቀፎች መከላከል እንደሚገባ ገልጸዋል። ለዚህም የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተሳትፎም ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። የ'ኢምፓዚ ፎር ላይፍ ኢንተግሬትድ ዲቨሎፕመንት አሶሴሽን' (ኤሊዳ) ዋና ዳይሬክተር ዚነት ይመር ማህበሩ ላለፉት 18 ዓመታት በሴቶች ትምህርት፣ በሰላም ግንባታ እና በኢኮኖሚ ማብቃት ላይ ሰፊ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሰው ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት እየጨመረ መምጣቱ የሴቶችን ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ተሳትፎ እየገደበው መሆኑን ጠቁመዋል። ይህንን ችግር ለመከላከልም የሁሉንም አካላት ትብብር፣ ቅንጅት እና አሳታፊ ምህዳር መፍጠር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል። ማህበሩም ይህንን የጥቃት አይነት በዘላቂነት ለመፍታት በተለያዩ አካባቢዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በስፋት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮጀክት አመራር፣ ትብብር እና የሀብት ማሰባሰብ ቡድን መሪ ሳምሶን ኒሻን ችግሩን ለመከላከል የሴቶች የፖሊሲ ክለሳ ተደርጎ በመጨረሻ ረቂቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ጉዳቱን ለመከላከል ጠንካራ መሰረት እንደሚጥል ገልጸው በስትራቴጂዎችም የተቀመጡ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ከዲጂታል እውቀት አንጻር ውስንነቶች መኖራቸውን አንስተው ተጠቂዎችም ሰፊ የግንዛቤ ክፍተት እንዳለባቸው ገልጸዋል። የሴት መብት ተሟጋች እና በሥርዓተ-ፆታ እኩልነት እንዲሁም በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ የምትሰራው ሰላማዊት ተዘራ ህጎች ቢኖሩም ሰፊ የአፈጻጸም ክፍተት መኖሩን አንስታለች። በቴክኖሎጂ እውቀት ረገድ ሰፊ ክፍተት መኖሩን ገልፀው፣ ችግሩን ለመቅረፍ ተከታታይነት ያላቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መሰጠት እንዳለባቸውም ተናግራለች። በሴቶች ላይ የሚደርስ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ ጥቃት ከፍተኛ የስነ ልቦና ጫናን የሚፈጥር መሆኑን የገለጸችው ደግሞ የሥርዓተ-ፆታ እኩልነት እና የማህበራዊ አካታችነት ጥናት ባለሙያ ሀና ለማ ናት። ድርጊቱ ዝቅ ተደርጎ ሳይታይ ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ገልፃለች።
በከተማው ዳሞታ ተራራን ምቹ የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የሚያስችሉ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Mar 6, 2026 48
ወላይታ ሶዶ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡-በወላይታ ሶዶ ከተማ የዳሞታ ተራራን ምቹ የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የሚያስችሉ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የከተማው ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መምሪያ በበኩሉ ግንባታውን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ገልጿል። መንግስት ለቱሪዝም ዘርፍ ትኩረት በመስጠት በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ቱሪዝምን ለማሳደግ ግብ ጥሎ እየሰራ መሆኑ የሚታወቅ ነው። የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደርም ከ20 በላይ ነባርና አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን የማልማትና ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡ የከተማው ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሪት ወይንሸት መና ለኢዜአ እንደገለጹት ዳሞታ ተራራን ምቹ የቱሪዝም መዳረሻ ማድረግ የሚያስችሉ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በዳሞታ ተራራ ላይ የተጀመረው የ7ሺህ 187 የደረጃ መወጣጫ ኢኮ ቱሪዝም ሳይት ግንባታ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ግንባታው በከተሞች አንድ የቱሪዝም መዳረሻ የማልማት ውጥን አካል መሆኑን የገለጹት ሃላፊዋ ሲጠናቀቅም የከተማዋን የቱሪስት ፍሰት በመጨመር ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ያሳድጋል ብለዋል። የከተማው ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መምሪያ የከተማ የተቀናጀ መሠረተ ልማት ሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ አስራት ዳዊት በበኩላቸው፣ የዳሞታ ኢኮ ቱሪዝም ሳይት የደረጃ መወጣጫ ግንባታ በሦስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ እየተገነባ ነው ብለዋል፡፡ የመጀመሪያውን ዙር ግንባታ በ90 ቀናት ለማጠናቀቅ ከተቋራጩ ጋር ውል በመግባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የመወጣጫ ደረጃው በጠቅላላው 5 ነጥብ 3 ኪሎ ሜት ርዝመት ያለው ሲሆን ለቱሪስቶች አገልግሎት የሚሰጡ ሌሎች መዝናኛ ቦታዎችና ተጨማሪ የመንገድ ግንባታን ያካተተ መሆኑም አመልክተዋል። ለመጀመሪያ ዙር ግንባታ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የጠቆሙት አስተባባሪው፣ ለልማቱ በአጠቃላይ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መያዙን ጠቅሰዋል። ግንባታው ሲጠናቀቅ ለቱሪስት ፍሰትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ካለው ጥቅም አንፃር በልዩ ትኩረት እየተመራ መሆኑንም አስታውቀዋል። የሳይቱ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ምሽት ጭምር እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ግንባታውን የሚያከናውነው ሥራ ተቋራጭ አንጆኒዮ ኮንስትራክሽን ሳይት መሀንዲስ መኮንን ተስፋዬ ናቸው፡፡ በግንባታ ሳይቱ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው አቶ ተገኝ ፉርቻካ እና አቶ ኦሎሞ አሰፋ የግንባታው መጀመር የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል፡፡ የቱሪዝም መዳረሻው ሲጠናቀቅ ለአካባቢው ተጨማሪ ዕድልና ተስፋ ይዞ እንደሚመጣ በማመን ሥራቸውን በአግባቡ እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ በፈተናዎች ጸንታ የቆመችው በማይበገረው የሠራዊታችን ተጋድሎ ነው -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Mar 6, 2026 82
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በታሪኳ በፈተናዎች ጸንታ የቆመችው በማይበገረው የሠራዊታችን ተጋድሎ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የኢትዮጵያ ሠራዊት ሙዚየም የጀግንነታችን ማኅደር፣ የልዕልናችን ምስክር ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪኳ በፈተናዎች ጸንታ የቆመችው በማይበገረው የሠራዊታችን ተጋድሎ እንደሆነም ተናግረዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በጃንሜዳ አካባቢ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሠራዊት ሙዝየም መጎብኘታቸውን ገልጸው፤ በሙዝየሙ የዘመናት የጀግንነት ጉዞ የሚመሰክሩ ህያው አሻራዎችን መመልከታቸውን ጠቁመዋል። ከ1950ዎቹ ጀምሮ እንዲቋቋም ሲታለም የቆየው ይህ የጦር መዝየም፣ በፖለቲካዊ ውሳኔዎች ብቅ እልም ሲል ቆይቶ ዛሬ በለውጡ መንግሥት ቁርጠኝነት ተቋማዊ ቁመና ተላብሶ እውን መሆኑን ነው ያነሱት። ይህ ስኬት ለሚገነባው ግዙፍ ብሔራዊ የሠራዊት ሙዝየምም እንደ ማዕዘን ድንጋይ የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል። ከዓድዋ ዘመን በፊት የነበሩ ብርቅዬ መሣሪያዎችና የነገሥታቱ ትጥቆችን ጨምሮ በሙዚየሙ ያሉት የጦር ታሪክና ቅርሶች የጀግኖቻችንን ታሪክ የሚዘክሩ ናቸው ብለዋል። ከ1900 ጀምሮ ያለውን ዘመናዊ የተቋም ግንባታ፣ የጦር መሣሪያዎች ዝግመተ ለውጥና መከላከያችን የደረሰበትን አስደናቂ የምህንድስና ጉዞ የሚያስቃኘው ይህ ማዕከል፤ ለሠራዊቱና ለትውልድ ታሪክን፣ ዕውቀትንና መነሳሳትን የሚያስታጥቅ መሆኑንም ነው ያመለከቱት። በሙዝየሙ፣ ከትናንቱ እንማርበታለን፤ ዛሬን እንገመግምበታለን፤ ለነገ ደግሞ እናቅድበታለን። አፍሪካውያንና መላው በፀረ ቅኝ አገዛዝ የታገለ የዓለም ሕዝብ ሁሉ ይሄንን ሙዝየም በመመልከት የራሱን ታሪክ እንዲያደንቅ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግብዣ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ሠራዊት የታሪካችን ኩራት፣ ከሀገር አልፎም በዓለም ስሙ ከፍ ብሎ የሚነሳ የሰላም ዘብ ነው ብለዋል። የታሪካችን ድምቀት የሆነው የሠራዊታችን ገድል ለትውልድ እንዲሸጋገር በዘመናዊ መንገድ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ይበል የሚያሰኙ በመሆናቸው፤ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል ሱሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።
ሴት የዩኒቨርሲቲ ምሁራን በሀገሪቱ የጾታ እኩልነት እንዲከበር ያበረከቱት አስተዋጽኦ ጉልህ ነው
Mar 6, 2026 82
ጎንደር፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡- ሴት የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ትውልድን ከመቅረጽ ባሻገር በሀገሪቱ የጾታ እኩልነት እንዲከበር ያበረከቱት አስተዋጽኦ ጉልህ ነው ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ከይረዲን ገለጹ፡፡ የጎንደር ዩኒቨርሰቲ 50 አመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ በሚል መሪ ሀሳብ ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በፓናል ውይይት አክብሯል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት ሚኒስትር ዴኤታዋ ሴት ምሁራን በእውቀት የዳበረ ትውልድን በመቅረጽ ረገድ በትምህርቱ ዘርፍ ገንቢ ተግባራትን አከናውነዋል፡፡ ሴት ምሁራን የሴቶች እኩልነትና መብቶች እንዲከበሩ ግንባር ቀደም ሚና መጫወታቸውን ጠቁመው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትም የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ በሀገሪቱ በምርምሩ ዘርፍ የላቀ አበርክቶ ያላቸው የሴት ምሁራን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል። በሀገር ግንባታው ዘርፍ የሴት ምሁራን ተሳትፎ የላቀ ሚና እንዳለው አመልክተው የሴት ምሁራን የሴቶችን ችግር በመፍታት ረገድ ተሳትፏቸው ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሳሁን ተገኝ (ዶ/ር) ሴቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሰው ልጆች እኩልነት፣ ለፍትህ፣ ለዴሞክራሲና ለሰላም ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ሴቶችን በትምህርት ከማብቃት ጀምሮ በምርምርና በሃላፊነት የሙያ ደረጃዎች እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል ስርአት ዘርግቶ ለተግባራዊነቱ እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ ሴቶች በሳይንስና ቴክኖሎጂ አንዲሁም በአዳዲስ ፈጠራና ግኝቶች ዙሪያ እውቀታቸውንና ክህሎታቸውን ከፍ የሚያደርጉ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን በመከተል ፍሬያማና ውጤታማ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ሴት ምሁራን ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎችን በማከናወን ሴቶች እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆኑበትን አውድ መፍጠር አለባቸው ያሉት ደግሞ የአማራ ክልል ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ብርቱካን ሲሳይ ናቸው፡፡ መንግስት ሴቶች በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካው ዘርፍ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ አንዲሆኑ አስቻይ ሁኔታዎችን በመፍጠር ረገድ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሴት መምህራን ተመራማሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት የዝቤ ካሳ (ዶ/ር ) ማህበሩ ሴት ተማሪዎችን በማብቃት በተሰማሩበት መስክ ውጤታማና ስኬታማ እንዲሆኑ የድርሻውን እያበረከተ ይገኛል ብለዋል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን አስመልክቶ ዩኒቨርሲቲው ባዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ የዩኒቨርሲቲው ሴት ምሁራንን ጨምሮ የፌደራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
ኢኮኖሚ
በክልሉ በመሬት አስተዳደር ዘርፍ ህገወጥነትን ለመከላከል በተሰራ ሥራ ከ10 ሺህ በላይ የመሬት ይዞታዎች ህጋዊ ተደርገዋል
Mar 6, 2026 60
ወላይታ ሶዶ፤የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በመሬት አስተዳደር ዘርፍ የሚስተዋሉ ህገ ወጥነቶችን ለመከላከል በተሰራ ሥራ ከ10 ሺህ በላይ ይዞታዎችን ህጋዊ ማድረግ መቻሉ ተገለጸ። የክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ በከተሞች ማስፋፊያ አካባቢ በጊዜያዊ የመሬት መጠቀሚያ ሠርተፊኬት አሰጣጥ፣ በህገ ወጥ የመሬት ወረራ እና ግንባታ መከላከል ላይ ያተኮረ የአቅም ማሳደጊያ መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል። የቢሮው ምክትልና የመሬት ይዞታ መረጃና ምዝገባ ዘርፍ ኃላፊ ዳንኤል ዳሌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት ቢሮው ከተቋቋመ ጀምሮ በመሬት ዘርፍ የሚስተዋሉ ህገ ወጥነቶችን ለመከላከል ግብ ጥሎ እየሰራ ነው። ለዚህም የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ የህግ ማዕቀፎችን መተግበር የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ገልጸው፣ በማስፋፊያ አካባቢም ጊዜያዊ የመጠቀሚያ ሰርተፍኬት በመስጠት ህገ ወጥነትን ለመከላከል እየተሰራ ነው ብለዋል። የመሬት ሀብት አስተዳደርን በሳይንሳዊ ዘዴ (በካዳስተር) በመምራት የመንግስትንና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል። በክልሉ የመሬት አስተዳደር ዘርፍ የሚስተዋሉ ማጭበርበሮችን ለመከላከል በተሰራው ሥራ እንደየመጠናቸው ከ53 ሺህ በላይ ህገወጥ ይዞታዎች መለየታቸውን የገለጹት ደግሞ የቢሮው ምክትልና የመሬት ልማትና አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ ኢንጂነር ፍሬው ፍሻለው ናቸው። ከነዚህ መካከል 10 ሺህ ይዞታዎችን ህጋዊ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው፣ ከህገ ወጦች የተወረሰ ከ29 ሄክታር በላይ መሬትም ወደ መሬት ባንክ እንዲገባ ተደርጓል ብለዋል። ቢሮው ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ቢሆነውም የተበታተኑ የአሰራር ስርዓቶችን ወደ አንድ የአሰራር ማዕቀፍ በማምጣት ዘርፉን ለማዘመን በተደረገ ጥረት ለውጥ እየታየ መምጣቱንም ጠቁመዋል። ባለድርሻ አካላትም በመሬት ሀብት ቆጠራ፣ ምዝገባና መረጃን በማዘመን፣ ብልሹ አሰራሮችን በመከላከልና መልካም አስተዳደርን በማስፈን ላይ እንዲያተኩሩ አስገንዝበዋል። በዘርፉ የሚስተዋለውን ሌብነትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ተባብሮ መስራት በማስፈለጉ መድረኩ መዘጋጀቱንም ኢንጂነር ፍሬው ጠቁመዋል። የወላይታ ዞን መሬት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምራት በለጠ በበኩላቸው እንዳሉት በዘርፉ የሚስተዋሉ የአሰራር ብልሽቶች መንግስትን ከፍተኛ ሀብት ሲያሳጡ ቆይተዋል። በዞኑ ሕገ ወጥ የመሬት ወረራ ለመከላከል በተደረገው ጥረት በአጭር ጊዜ ውስጥ 351 ሄክታር በላይ የገጠር መሬት ወደ ህጋዊ ቋት እንዲገባ መደረጉን ተናግረዋል። በጋሞ ዞን መሬት አስተዳደር መምሪያ የመሬት ዝግጅትና መልሶ ማልማት ቡድን መሪ ቀሲስ ይታገሱ በቀለ በበኩላቸው እንዳሉት በዞኑ መሬትን ከህገ ወጦች ለመጠበቅ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ ተገብቷል። በዞኑ ባሉ አምስት ከተማ አስተዳደሮች በተደረገ ቁጥጥር በማስፋፊያ አካባቢዎች በህገ ወጥነት የተያዙ ከ5 ሺህ በላይ ይዞታዎች ህጋዊ ማድረግ መቻሉን ገልጸው፣ በቀጣይም ይሄ ሥራ ይጠናከራል ብለዋል። ለሁለት ቀናት እየተካሄደ ባለው በዚህ መድረክ ላይ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በከተማው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ዘርፉን አነቃቅቷል
Mar 6, 2026 55
ደብረ ማርቆስ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፡- በደብረ ማርቆስ ከተማ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የባለሀብቱን የማልማት ፍላጎት ከማነሳሳት ባለፈ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማነቃቃቱን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ። በከተማው በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተከናወኑ ተግባራት በመስክ የተገበኙ ሲሆን የምክክር መድረክም ተካሄዷል። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የኢንዱስትሪ ዘርፉ ለከተማዋ ኢኮኖሚያዊ እድገት መነቃቃት ያለው አስተዋጾው የጎላ ነው። በከተማዋ በርካታ ባለሃብቶች በኢንዱስትሪ ዘርፍ መሰማራተቸውን ገልጸው፤ በተሰማሩበት መስክ ውጤታማ እንዲሆኑም በመንግስት በኩል ጠንካራ ክትትልና እገዛ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በከተማዋ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የባለሃብቱን የማልማት ፍላጎት ከማነሳሳት ባለፈ የኢንዱስትሪ ዘርፉ እንዲነቃቃ በማድረግ በኩል የጎላ አበርክቶ እንዳለው ተናግረዋል። የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ተመስገን ተድላ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተቀዛቅዞ የነበረውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እንዲነሳሳ አደርጓል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት መጠን 20 በመቶ መጨመሩን እና ወደዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶች ቁጥር መበራከቱን ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ በዘርፉ የሚስተዋሉ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ባለሃብቱን ባሳተፈ መንገድ መፍታት ተችሏል ብለዋል። በከተማው በዘርፉ ከተሰማሩ ከ250 በላይ ኢንዱስትሪዎች ከ90 በላይ የሚሆኑት ወደ ማምረት የገቡ ሲሆን ቀሪዎቹ በማሽን ተከላ ሂደት ላይ ናቸው ብለዋል። በኢንዱስትሪው ዘርፍ የተሰማሩት ባለሃብቶች ከ33 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ መሆኑም ተገልጿል። የመድረኩ መዘጋጀትም በማምረትም ሆነ በየደረጃው ያሉትን ፕሮጀክቶች ያለባቸውን ተግዳሮት በመለየት መፍትሄ ለማፈላለግና የከተማዋን ኢንቨስትመንት ለማሳደግ ታሳቢ ያደረገ ነው። በመድረኩ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና በኢንዱስትሪው ዘርፍ የተሰማሩ ባለሃብቶች ተሳትፈዋል።
የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና የኢትዮጵያን የንግድ ምህዳር ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታላቅ ዕድል ነው
Mar 6, 2026 71
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና (AfCFTA) የኢትዮጵያን የንግድ ምህዳር ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታላቅ ዕድል ከመሆኑም ባለፈ ከጎረቤት አገራት ጋር ያለውን የንግድ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ ቀነኒሳ ለሚ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና መመስረት ለኢትዮጵያ ነጋዴዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችን ያስገኛል ብለዋል፡፡ በዚህም ነጋዴዎች ምርታቸውን በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ያለ ታሪፍና የንግድ መሰናክል የመሸጥ ዕድል እንደሚያገኙ ተናግረዋል፡፡ በህጋዊ ውድድር ውስጥ ማለፋቸው ነጋዴዎች ራሳቸውን ዘወትር እንዲያሻሽሉ ያደርጋል ያሉት ዋና ጸሐፊው አዳዲስ አሰራሮችን እንዲከተሉና ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ ምቹ ዕድል እንደሚፈጠርም ገልጸዋል፡፡ የገበያው መከፈት ከሌሎች አፍሪካውያን ነጋዴዎች ጋር የንግድ ስልቶችን ለመቅሰም ትልቅ አጋጣሚ እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡ የሀገሪቱ የንግድ ህጎች ከአህጉራዊው ስርዓት ጋር መጣጣማቸው የውጭ ኢንቨስተሮችን ይስባል፤ ይህም ለዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር ለሀገራዊ ብልጽግና መሰረት ይሆናል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በዕቃ ንግድ ፕሮቶኮል ላይ ትኩረት አድርጋ እየሰራች መሆኑን ጠቅሰው፤ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከኬኒያና ከሶማሊያ ጋር የንግድ ልውውጥ መጀመሩንም ገልጸዋል፡፡ ይህም ከጎረቤት አገራት ጋር ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ጠቅሰዋል፡፡ ምክር ቤቱ ነጋዴዎች ያላቸውን ጸጋ ለይተው እንዲያውቁና በምርቶቻቸው ላይ እሴት በመጨመር በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ስልጠናና ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ አስችሏል
Mar 6, 2026 67
ጎንደር፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ) ፡- የሌማት ትሩፋት መርሀግብር የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ አስችሏል ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ከይረዲን ገለጹ። 50 አመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበጸገች ኢትዮጵያ በሚል መሪ ሀሳብ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ በጎንደር ከተማ ስኬታማ የሆኑ ሴቶች የልማት ተሳትፎ የመስክ ጉብኝት ተካሂዷል። ሚኒስትር ድኤታዋ በጉብኝቱ ላይ በሰጡት መግለጫ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደ ሀገር የተነደፉ ስትራቴጂዎች ውጤታማነታቸው ከፍተኛ ነው። የሌማት ትሩፋት መርሀግብር የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም በመገንባት ሀብት አፍርተው ወደ ባለሀብትነት የሚሸጋገሩበትን እድሎች መፍጠሩን ተናግረዋል። በዚህም በርካታ ሴት ባለሀብቶችን በመፍጠር ምርታቸውን ከሀገር ውስጥ ባለፈ ለውጭ ገበያ በማቅረብ በሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንደቻሉ አመልክተዋል። በክልሎች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረው የሴቶች የልማት ህብረትም እንደ ሀገር ሞዴል እየሆነ መምጣቱን ጠቁመዋል። በጎንደር ከተማም በተቀናጀ የግብርና ልማት እንዲሁም በሴቶች የልማት ህብረት ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገባቸውን ጠቅስዋል። የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ብርቱካን ሲሳይ በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሴቶችን ህይወት ለመቀየር የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል። እለቱን ምክንያት በማድረግ የተካሄደው የመስክ ጉብኝት ውጤታማ የሆኑ ሴቶችን ተሞክሮ ለማስተዋወቅና ለማበረታታት ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። በጎንደር ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሀግብር በመሳተፍ በ59 ዶሮ የጀመሩት የዶሮ እርባታ አሁን ላይ 47ሺ ማድረስ እንደቻሉ የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ ጽላተማርይ ተመስገን ናቸው። ከዶሮ እርባታ በተጨማሪ በንብ ማነብና በኩሬ አሳ እርባታ መሰማራታቸውን ጠቁመው የእንቁላልና የማር ምርት ለዉጪ ገበያ ማቅረብ መጀመራቸውን ተናግረዋል። በተሰማሩባቸው መስኮች ለ136 ሰዎች የስራ እድል መፍጠራቸውንም ገልጸዋል። በከተማው በተቀናጀ የወተት ሀብት ልማት የተሰማሩት ወይዘሮ ሰብለ ማሩ በ15ሺ ብር ካፒታል የጀመሩት የወተት ልማት ስራ አሁን ላይ 80 የወተት ላሞች ባለቤት በመሆን ካፒታላቸውን 12 ሚሊዮን ብር ማድረስ ችለዋል። ለ50 ሰው የስራ እድል በመፍጠር በየቀኑ 500 ሊትር ወተት ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ እንደሆኑ ተናግረዋል። እለቱን ምክንያት በማድረግ በሴት ነጋዴዎች የተዘጋጀ ባዛር ተመርቆ ተከፍቷል። በጉብኝቱ ላይ የፌደራልና የክልሉ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው ሴቶች ተሳትፈዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢንስቲትዩቱ የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ ምርምሮችን እያከናወነ ነው
Mar 6, 2026 139
አዳማ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ የጥናትና ምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ አስራት እንደገለጹት፤ ተቋሙ በኦሮሞ ባህል፣ እሴት፣ ስነ-ጥበብ፣ ታሪክ፣ ቋንቋና እድገት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። ወጣቶች መልካም ስብዕናን ተላብሰው ለሀገር ልማት እና እድገት እንዲተጉ የባለድርሻ አካላት ሚና ሊጠናከር ይገባል ይህንንም ውጤታማ ለማድረግ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ከሚገኙ ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ከቱሪዝም ኮሚሽን፣ ከባህል ጥናት ማዕከል እንዲሁም ከወጣቶችና ስፖርት ቢሮዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ እስካሁን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ከ70 በላይ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ከእነዚህም መካከል በታሪክ፣ በቋንቋና በባህል ላይ ያተኮሩ ከ30 በላይ መጻሕፍት ታትመው ለማህበረሰቡ ተደራሽ ሆነዋል ብለዋል። እነዚህ ስራዎች በተለይም የወጣቶችን የማንበብ ባህል ለማጠናከርና ሁለንተናዊ ስብዕናቸው እንዲገነባ ለማስቻል ትልቅ ድርሻ እንዳላቸውም አመልክተዋል። የጥናት ውጤቶቹንና የመጻሕፍት ዝግጅቱን አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች፣ ስራው በትውልዱ ላይ የሚታየውን የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላት እንደሚረዳ ገልጸዋል። ወጣት ስራጅ አህመድ እንደገለጸው፣ ንባብ ወጣቶች ስለ ማህበረሰቡ ስብዕናና ባህል እንዲያውቁ ያደርጋል። የገዳ ስርዓት መሰረታችንና ማንነታችን ነው ያለው ወጣት ስራጅ፣ ስለ ስርዓቱና ስለ ኦሮሞ እሴቶች በቂ እውቀት ለማግኘት የንባብ ባህላችንን ማጎልበት ይገባናል ብሏል። ተተኪው ትውልድ ስራን ከመናቅ ወጥቶ በልማት ስራዎች ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለበትም ነው የገለጸው።
የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ “ንዋይ” የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያን ይፋ አደረገ
Mar 5, 2026 134
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (ESX) የካፒታል ገበያን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል “ንዋይ” የተሰኘ የሞባይል ግብይት መተግበሪያ ዛሬ ይፋ አድርጓል። መተግበሪያው በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ማንኛውም ግለሰብ በሞባይል ስልኩ በመጠቀም በአክሲዮን እና በዕዳ ሰነዶች ግብይት ላይ በቀጥታ እንዲሳተፍ እድል የሚሰጥ ነው። የኢትዮጵያ የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን እስማኤል (ዶ/ር) በመተግበሪያው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ እንደተናገሩት፤ "ንዋይ" ገበያውን በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እጅ ላይ ተደራሽ ያደርገዋል። መተግበሪያው ባለሀብቶች በማንኛውም ጊዜና ቦታ ሆነው በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ውስጥ በቀጥታ እንዲሳተፉ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው የሰነድ ግዢና ሽያጭ ትዕዛዞችን በስልክ ማስተላለፍና መፈጸም እንሚያስችልም ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተህልቁ በበኩላቸው በርካታ ሀገራት ወደዚህ ዓይነት የቴክኖሎጂ ሥርዓት ለመድረስ ረጅም ጊዜ እንደወሰደባቸው አስታውሰዋል። ኢትዮጵያ ግን ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ በመማር በአጭር ጊዜ ውስጥ ዘመናዊ የገበያ ሥርዓት መገንባቷን ገልጸዋል። ይህ ሥርዓት ልዩ የሚያደርገው አካታችነቱ ነው ያሉት ዳይሬክተሯ በሁሉም የሀገሪቱ ጫፍ ያሉ ዜጎች የኢንቨስትመንት አካውንት በመክፈት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ መንግስት ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው ግልጽና ተገማች የሆኑ ህጎች መውጣታቸው ለዚህ ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥራ አስፈጸሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር)፣ ገበያው ሁሉም ዜጋ በአቅሙ ልክ የሚሳተፍበት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። እንደ ቴሌ ብር እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) መተግበሪያዎች ያስመዘገቡት ስኬት ለ"ንዋይ" ውጤታማነት እንደ ማሳያ እንደሚጠቀስም ገልጸዋል። መተግበሪያውን በአሁኑ ወቅት በአንድሮይድ (Android) እና በአይኦኤስ (iOS) ስልኮች ላይ ለመጫን ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የካፒታል ገበያ ባለቤት ማድረግ ግብን ለማሳካት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያን ዲጂታል መሠረተ-ልማት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ስምምነት ተፈረመ
Mar 5, 2026 127
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮ ቴሌኮም የኔትወርክ ማስፋፊያን በማከናወን እና በማዘመን የኢትዮጵያን ዲጂታል መሠረተ-ልማት ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ከኤሪክሰን ኩባንያ ጋር ተፈራረመ። ስምምነቱ በኤሪክሰን የኔትወርክ አሥተዳደር ቀጣና ውስጥ በሚገኙ 1 ሺህ 500 የሞባይል ጣቢያዎች ላይ የማስፋፊያ፣ የማሻሻያ፣ የ4ጂ ንጣፍ እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የመገንባት ሥራዎችን ያካትታል ተብሏል። ይህ ሁለንተናዊ የማዘመን ኢኒሼቲቭ የኔትወርክ ሽፋንን፣ ጥራትንና ዐቅምን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሻሽል መሆኑን የኢትዮ ቴሌኮም መረጃ አመላክቷል። በዚህም ነባር መሠረተ ልማቶችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመተካት፤ የ4ጂ ሽፋን እና ዐቅምን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድግ መሆኑ ተጠቁሟል። የ5ጂ ተደራሽነትንም በማስፋት ለዘመናዊ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያስፈልገውን ከፍተኛ የፍጥነት ኮኔክቲቪቲ ዕውን ለማድረግ ያስችላል ነው የተባለው። በተለይም ፕሮጀክቱ 75 ለሚሆኑ የገጠር አካባቢዎች ተስማሚ የሆኑ የሞባይል ቴክኖሎጂ ሶሉሽኖችን ለማቅረብ እንደሚያስችልም ተመላክቷል። በተጨማሪም 502 ነባር የ3ጂ ጣቢያዎችን ለማዘመን እና ወደ ላቀ የ4ጂ ቴክኖሎጂዎች ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል። ፕሮጀክቱ በኤሪክሰን (Ericsson) የኦፕሬሽን ቀጣና ውስጥ 2 ነጥብ 8 ሚሊየን አዲስ የ4ጂ ኔትዎርክ የመሸከም ዐቅም ለመጨመር የሚያስችል ሲሆን፤ ይህም አጠቃላይ የኔትዎርክ ዐቅሙን ወደ 4 ነጥብ 1 ሚሊየን ለማድረስ ያስችላል ተብሏል። በተጨማሪም የኤልቲኢ (LTE) አገልግሎትን ወደ 157 ተጨማሪ ከተሞች በማስፋፋት፣ አጠቃላይ የኤልቲኢ አገልግሎት ተጠቃሚ ከተሞችን ቁጥር ወደ 276 ያደርሳል ብሏል ኢትዮ ቴሌኮም። ይህም ሽፋንን በ45 በመቶ በማሳደግ፤ በሪጂኑ ያለውን አጠቃላይ የሕዝብ ሽፋን 85 በመቶ ለማድረስ እንደሚያስችል ጠቁሟል። ስምምነቱ የኢትዮጵያውያንን የአኗኗር ዘይቤ፣ አሠራር እና ግብይት የሚያከናውኑበትን መንገድ ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገሩ የሚገኙ፤ እንደ ቴሌብር፣ ዘመን ገበያ እና ዘኔክሰስ ለመሳሰሉ ፕላትፎርሞች ድጋፍ ይሰጣል።
ማዕከሉ በተቋቋመ ስድስት ወራት ውስጥ ከ23 ሺህ በላይ ሰዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት አግኝተዋል
Mar 5, 2026 138
ድሬደዋ፣ የካቲት 26/2018(ኢዜአ) :-የድሬዳዋ መሶብ የአንድ ማዕከል በተቋቋመ ስድስት ወራት ውስጥ ከ23 ሺህ በላይ ሰዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸው ተገለጸ። የማዕከሉ አስተባባሪ አቶ አወቀ ለገሰ ለኢዜአ እንደገለጹት በመስከረም 2018 ስራ የጀመረው ማእከሉ በ10 ተቋማት 28 አገልግሎቶች እየተሰጡ ነው። ማእከሉ ስራ ከጀመረ ወዲህ ከ23ሺህ በላይ ሰዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ማእከሉ ከወረቀት ንክኪ የፀዳ ዘመናዊ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህዝብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል። በተሰራው የእርካታ ዳሰሳ ጥናት ህብረተሰቡ በመንግስት አገልግሎት ከፍተኛ እርካታ ማግኘት እንደቻለ መረጋገጡን አመልክተዋል። በማዕከሉ የተሰባሰቡ ተቋማት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ተገልጋዮች ናቸው። ከተገልጋዮች መካከል አቶ አብዲ ቡሽራ እንዳሉት በማዕከሉ የሚሰጡት ዲጂታል አገልግሎቶች አስደሳች መሆናቸውን ገልጸዋል። በማዕከሉ የይዞታ ካርታ ለማውጣት መጥተው ፈጣን አገልግሎት በማግኘታቸው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ አጠናቀው ወደ ስራቸው መመለስ እንደቻሉ ተናግረዋል። ቀደም ሲል ተቋማት በተለያዩ አካባቢዎች ተበታትነው ስለሚገኙ አንድ አገልግሎት ለማግኘት እስከ ሳምንት ጊዜ እንደሚፈጅና ብዙ ድካም ይጠይቅ እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ በመጣው ለውጥ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ወይዘሮ ሰላማዊት ሐጎስ በበኩላቸው ግብር ለመክፈል ወደ ማእከሉ መምጣታቸውን ጠቁመው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ መጨረሳቸውን ተናግረዋል ። ወደ ማእከሉ ጉዳይ ለማስፈጸም መጥተው ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ አቶ ፍሰሐ ሰለሞን ናቸው። በማእከሉ ተቋማት በሚሰጡት ፈጣን አገልግሎት መደሰታቸውን ጠቁመው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመልክተዋል።
ስፖርት
ረቂቅ አዋጁ የስፖርት እድገትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል
Mar 6, 2026 57
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦የፌዴራል ስፖርት ልማትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ የስፖርት እድገትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ ገለጹ። ቋሚ ኮሚቴው በፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን ለማዳበር የሚያስችል የውይይት መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሂዷል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፤ የስፖርት ዘርፉ የሚመራበት ሁሉን አቀፍ የአሰራር ስርዓትና ህግ አለመኖሩን አንስተዋል። የለውጡ መንግስት ይህን ችግር ለመፍታት የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅቷል ብለዋል። ይህም ጠንካራ፣ ብቁና ጤናማ ትውልድን ለማፍራት፣ ስፖርት ከዜጎች የኑሮ ዘይቤ ጋር የተሳሰረ እንዲሆን አቅም እንዲፈጠር የሚያደርግ ነውም ብለዋል። መንግስት ባለፉት ስምንት ዓመታት የዘርፉን ስብራት ለማከም በከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን ጠቁመው፤ በዚህም ከ17 ሺህ በላይ አነስተኛና መካከለኛ ስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራ በመላ ሀገሪቷ መገንባት መቻሉን ገልጸዋል። ረቂቅ አዋጁ ስፖርት በተጠናከረ ህግና ስርዓት እንዲመራ በማድረግ የዘርፉን እድገት ለማፋጠን አቅም የሚፈጥር ነውም ሲሉ ሚኒስትሯ አክለዋል። በመድረኩ ላይ የተሳተፉ የዘርፉ ተዋናዮች የረቂቅ አዋጁ መዘጋጀት በሀገሪቱ የስፖርት ዘርፉ ውጤታማ እንዳይሆን ማነቆ የሆኑ አሰራሮችን ለመፍታት የሚያስችል እንደሆነ ገልጸው፤ ቢስተካከሉ ያሏቸውን ሀሳቦች አንስተዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱ ለዘርፉ እድገት አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። በረቂቅ አዋጁ ፌዴሬሽኖች ደረጃውን የጠበቀ የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራ ይገነባሉ የሚል ድንጋጌ መኖሩን ጠቁመው፤ ይህ የፌዴሬሽኖችን አቅም ታሳቢ ያደረገ መሆኑን መፈተሽ ያስፈልጋል ብለዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ ፍሬያማ ለማድረግ ከዓለም አቀፍ የስፖርት ህጎች ጋር በተናበበ መልኩ ሊሆን እንደሚገባ ምክረ ሀሳብ ሰጥተዋል። አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ረቂቅ አዋጁ እንደ ሀገር በስፖርት ዘርፉ ላይ የሚፈለገውን ውጤት ለማመጣት ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር በኩል ጉልህ አበርክቶ ይኖረዋል ብሏል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ ቋሚ ኮሚቴው የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ የተደራጀ እንዲሆን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ግብዓት ሲያሰባስብ መቆየቱን ገልጸዋል። የፌዴራል ስፖርት ልማትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ የስፖርት እድገትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድል ቀንቶታል
Mar 6, 2026 52
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይርጋጨፌ ቡናን 3 ለ 1 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ እፀገነት ግርማ፣ እሙሽ ዳንኤል እና ረድኤት አስረሳኸኝ ግቦቹን አስቆጥረዋል። አዳነች አስፋው ለይርጋጨፌ ቡና ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ትዕግሥት አዳነ የጨዋታው ኮከብ ተጫዋች በመሆን ተመርጣለች። በሊጉ 14ኛ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ44 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ንግድ ባንክ ከመሪው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ተደርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አዲስ አዳጊው ይርጋጨፌ ቡና በ11 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ ረድኤት አስረሳኸኝ በሊጉ ያስቆጠረቻቸውን ግቦች ብዛት ወደ 13 ከፍ በማድረግ በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክሩ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ዳግማዊት ሰለሞን (19 ግቦች) በመቀጠል ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። ዛሬ በተደረጉ የ17ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 1 ሲያሸንፍ ልደታ ክፍለ ከተማ እና ቦሌ ክፍለ ከተማ ሁለት አቻ ተለያይተዋል።
ኢትዮ ኤሌክትሪክ መሪነቱን ያጠናከረበት ድል አስመዘገበ
Mar 6, 2026 60
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 /2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት ኢትዮ ኤሌክትሪክ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 1 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዙፋን ደፈርሻ፣ ማህሌት ምትኩ እና ዳግማዊት ሰለሞን የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ዝናሽ ሰለሞን ለድሬዳዋ ከተማ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፋለች። የኢትዮ ኤሌክትሪክ ተጫዋቿ ዙፋን ደፈርሻ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። በሊጉ 15ኛ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ነጥቡን ወደ 46 ከፍ በማድረግ መሪነቱን አጠናክሯል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ19 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። የኢትዮ ኤሌክትሪክ ተጫዋቿ ዳግማዊት ሰለሞን በሊጉ ያስቆጠረቻቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 19 ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት መሪነቷን አጠናክራለች።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ልደታ ክፍለ ከተማ እና ቦሌ ክፍለ ከተማ ነጥብ ተጋሩ
Mar 6, 2026 64
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ልደታ ክፍለ ከተማ እና ቦሌ ክፍለ ከተማ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። በኤፍኤ ካፕ ሊቨርፑል ከዎልቭስ ጋር ይጫወታል በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሰብለወንጌል ወዳጆ እና ይታገሱ ተገኝወርቅ ለልደታ ክፍለ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ቃልኪዳን ሸዋነህ እና ዳሳሽ ሰውአገኝ የቦሌ ክፍለ ከተማን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። የልደታ ክፍለ ከተማዋ ሜሮን አበበ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። ውጤቱን ተከትሎ ልደታ ክፍለ ከተማ በ15 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ቦሌ ክፍለ ከተማ በ30 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
አካባቢ ጥበቃ
በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ ነው
Mar 6, 2026 91
ጋምቤላ ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ወይና ደጋማ አካባቢዎች በቀጣዮቹ ሶስት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለበልግ እርሻ አመቺ መሆኑን በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋምቤላ ክልል ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አስታወቀ። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል በኢንስቲትዩቱ የጋምቤላ ክልል የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋሁን ዓለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ወይና ደጋማ አካባቢ በቀጣይ ወራት የሚኖረው የበልግ ዝናብ ለእርሻ ስራ ተስማሚ ነው። በክልሉ ወይና ደጋማ የአየር ፀባይ ያለው የማጃንግ ዞን በቀጣዩቹ ሶስት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለእርሻ ስራና ለእንስሳት ግጦሽ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር የአየር ትንበያ መረጃ ያመለክታል ብለዋል። በተለይም በዞኑ ቀድመው ለሚዘሩ የሰብል ዓይነቶችና ለመኸር እርሻ ስራ ዝግጅት በቂ የዝናብ ስርጭት እንደሚኖር መተንበዩን አመላክተዋል ። በሌላ በኩል ደግሞ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት በክልሉ ቆላማ አካባቢዎች ጠንከር ያለ የሙቀት መጠን እንደሚኖር የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጸዋል። በመሆኑም የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር የውሃ መጠን መቀነስ ሊኖር ስለሚችል ህብረተሰቡ ውሃን በአግባቡ መጠቀም እንዳለበት ምክር ሃሳብ ሰጥተዋል። እንዲሁም ከሙቀቱ መጨመር ጋር ተያይዞ በሰዎች ላይ የቆዳ ሽፍታ ሊከሰት ስለሚችል ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል
Mar 5, 2026 97
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አስከፊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ሀገራት ለዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃል ኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም ገለጸ። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ተፈፃሚነት ያላት ቁርጠኝነት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንዳስቻላት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ተቋማዊ ልማት አማካሪ መንሱር ደሴ ገልጸዋል። ከየካቲት 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የአውደ ጥናት የምክክር መድረክ ተጠናቋል። በአውደ ጥናቱ ማጠናቀቂያ ላይ የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የአፍሪካ አስተባባሪ ጆንኪ ቴኑ፤ የአካባቢና የሥነ-ምኅዳር ደኅነንት ለማስጠበቅ ትብብርን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል። አውደ ጥናቱም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ተግባራዊ የተደረጉ መርሃ ግብሮችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ስኬታማ የልምድ ልውውጥና ግብዓት እንደተገኘበት ገልጸዋል። በፖሊሲዎችና የትኩረት መስኮች የተደረገው ውይይትም የዕውቀት ሽግግር የተደረገበት መሆኑን ተናግረዋል። ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም የመንግሥታቱን ድርጅት የአየር ንብረት ስምምነት መነሻ በማድረግ ለተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ እያቀረበ እንደሚገኝ አንስተዋል። ሀገራትም የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አስከፊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአካባቢ ጥበቃ ተቋም ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚያግዝ አረጋግጠዋል። በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ተቋማዊ ልማት አማካሪ መንሱር ደሴ በበኩላቸው፤ በአውደ ጥናቱ ከ14 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 150 ሙያተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ዓለም አቀፍ ስምምነትና ቃልኪዳኖች ትግበራ ያላት ቁርጠኝነት በልማት አቅጣጫዎቿ ላይ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን አስረድተዋል። በአውደ ጥናቱም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም በተደረገ ድጋፍ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት መቅረባቸውን ተናግረዋል። ከሀምሌ ወር ጀምሮ ለአራት ዓመታት የሚተገበረው የዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም መርሃ ግብርም ከኢትዮጵያ የልማት አቅጣጫዎች ጋር ተጣጥመው እንደሚተገበሩ አንስተዋል።
በምስራቅ ሸዋ ዞን የአካባቢውን ሥነ ምሕዳር መሠረት ያደረጉ ችግኞች እየተዘጋጁ ነው
Mar 4, 2026 195
አዳማ ፤ የካቲት 25/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የአካባቢውን ሥነ ምሕዳር መሠረት ያደረጉና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን የማፍላት ስራ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በምስራቅ ቦረና ዞን የእንስሳት መኖ እጥረት እንዳያጋጥም የመኖ ልማት ስራ ከተፋሰስ ጥበቃ ጋር ተቀናጅቶ እየተከናወነ ነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ሃገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ሐምሌ 2011 ዓ.ም መጀመሩ ይታወቃል። በምስራቅ ሸዋ ዞን ግብርና የጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዞኑ 11 ወረዳዎች ባሉ የችግኝ ማፊያ ጣቢያዎች ለመጪው ክረምት የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ተጀምሯል። ችግኝ ጣቢያዎቹ ለአረንጓዴ አሻራ ዘመቻው የተለያየ ዝርያ ያላቸው ችግኞችን አፍልቶ በማቅረብ ረገድ እያበረከቱ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን አስታውሰዋል። ዘንድሮም ለማዘጋጀት ከታቀደው ከ284 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ውስጥም 241 ነጥብ 4 ሚሊዮን ችግኞችን የማፍላት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። ቀሪ ችግኞችን የማፍላት ሥራም እስከ መጪው ግንቦት ወር ድረስ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በችግኝ ዝግጅቱም በአብዛኛው የአየር ንብረት መዛባትን ለመከላከል ለሚያገለግሉ የደን እና ጥምር ደን ዝርያዎች ትኩረት የተሰጠ መሆኑን አስረድተዋል። በተጨማሪም ለአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን የሚያስገኙና እና ለምግብነት የሚውሉ 26 ነጥብ 7 ሚሊዮን የፍራፍሬ ችግኞችን ያካተተ የዘር ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል። የዘንድሮ ዓመት የችግኝ ተከላ የአካባቢውን ሥነ ምሕዳር መሠረት በማድረግ የሚከናወን መሆኑን ጠቁመው በዞኑ ባለፉት ዓመታት ከተተከሉ ችግኞች ከ85 በመቶ በላይ መጽደቃቸውን አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅትም የተተከሉ ችግኞችን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ የመጠበቅና የመንከባከብ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ነው ያረጋገጡት። በዘንድሮው ዓመት በዘርፉ የተቀመጠውን እቅድ ለማሳካትም የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ተቆፍረው መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት ይጠበቅባቸዋል
Mar 3, 2026 198
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት መገንባት እንደሚጠበቅባቸው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ገለጸ። "በምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የሚቋቋም ግብርናን ማስፋፋት" በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ቀጣናዊ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በኢጋድ፣ የዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ፣ የሥርዓተ ምግብ ፕሮግራም ለምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ፣ የደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምርና ልማት ማስተባበሪያ ትብብር በተዘጋጀው መድረክም የግብርና ማሻሻያ ምክረ ሀሳቦችን እንደሚያፈልቅ ይጠበቃል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ተወካይ ዳህር ኤልሚ፤ በአየር ንብረትና በሥነ-ምኅዳር ደኅንነት የሚከሰት ለውጥ የግብርና ምርታማነት ላይ ጫና እያሳደረ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለው የአፈር መራቆት፣ ድርቅ፣ ጎርፍ፣ ዝናብ እጥረትና በርሃማነት የምስራቅ አፍሪካ የግብርና ምርታማነትና የምግብ ፍጆታ ላይ አሉታዊ ጫና እንደሚያሳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የቀጣናው ሀገራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አስተማማኝ የግብርና ሥርዓት ለመገንባት የቴክኖሎጂ፣ የግብዓትና የመረጃ ትንተና አቅም መገንባት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣንም የቀጣናውን ሀገራት የግብርና ምርታማነት የሚያሻሽል የአየር ሁኔታ የመረጃ ትንተና ተደራሽ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢኒስቲትዩት የተፈጥሮ ሃብትና የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም ፕሮግራም ዳይሬክተር አወቀ ሙሉዓለም በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ሥርዓት ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችም የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ የአርሶና አርብቶ አደሩን የግብርና ምርታማነት እያሳደገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዓለም ባንክ ከፍተኛ የግብርና ባለሙያ ቲም ሮበርትሰን፤ የግብርና ምርታማነት የሚያዘምኑ የፋይናንስና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በማስፋት የቀጣናው ሀገራት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር የኢጋድና የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦዌን በበኩላቸው፤ የግብርና ምርታማነትን ማረጋገጥ ለአፍሪካ ዕድገትና ብልጽግና ወሳኝ ነው ብለዋል። የቀጣናውንና አፍሪካን የግብርና ሥርዓት ለማዘመን በሚደረገው ጥረትም የኒውዝላንድ መንግስትና የልማት አጋሮች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች፣ ፖለሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮችና ተመራማሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በሰላምና ደኅንነት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Mar 5, 2026 94
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፦ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም እና ደኅንነት ያላቸውን ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የኢጋድ የሰላም እና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ውይይቱን ያደረጉት የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁን (ዶ/ር) በመወከል ነው። ውይይቱ ኢጋድ እና የአፍሪካ ኅብረት በቀጣናው ሰላም፣ ደኅንነት እና መረጋጋት ላይ ያላቸውን የጋራ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው። ሁለቱ ወገኖች የጋራ የተግባር ምላሽ ለመስጠት እና ስትራቴጂካዊ ትብብራቸውን ለማጎልበት ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የመንግሥታቱ ድርጅትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ ይገባል
Mar 4, 2026 195
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃዎች ሊተገብሩ እንደሚገባ ተገለጸ። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከጃፓን ኤምባሲ ጋር በመሆን የተባበሩት መንግሥታት ሪፎርም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል። የመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና ዓለምአቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩ ቢሆኑም በተቋማዊ አወቃቀር ሥርዓት ላይ አፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ያገለሉ ናቸው። የአማኒ አፍሪካ ዳይሬክተር ሰለሞን አየለ ደርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት መዋቅር የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና የሚያረጋግጥ የሪፎርም እርምጃ ሊወስድ ይገባል። በተቋማቱ የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥም ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ተከታታይ ሥራ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል። የአህጉሪቱ አባል ሀገራትና ከሌሎች ሀገራት ጋር ትብብርን በማጠናከር የአፍሪካን የዓለምአቀፍ ተቋማት ፍትሐዊ ውክልና ማስከበር የሚስችል መዋቅራዊ የሪፎርም እርምጃ እንዲወሰድ መስራት ይገባል ብለዋል። የአማኒ አፍሪካ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ተቋም የአፍሪካን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በአፍሪካ ሕብረትና የአፍሪካ ዳያስፖራ ጉዳዮች ላይ በጥናትና ምርምር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የጋና አምባሳደር ሮበርት አፍሪይ(ዶ/ር)፤ አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ተቋማት ያቀረበችው ፍትሐዊ የውክልና ጥያቄ ችላ በመባሉ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ የሌላት ብቸኛ አህጉር አድርጓታል ብለዋል። ለዚህም የመንግስታቱ ድርጅት አፍሪካ በተሸከመችው የጸጥታው ምክር ቤት የሥራ ጫና ልክ ውክልና የሚያስገኛትን የሪፎርም እምርጃ መውሰድ እንዳለበት ገልጸዋል። በአፍሪካ ሕብረት የጃፓን ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኖቦሩ ሴኪጉቺ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በመንግስታቱ የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ላይ ፍትሐዊ ውክልና ሊሰጣት ይገባል ብለዋል። ጃፓንም አፍሪካ በመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትና በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የሚኖራትን ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ድጋፏን እንደምታጠናክር አረጋግጠዋል። ጃፓንና የጂ-4 አባል ሀገራት የአፍሪካን ዓለም አቀፍ ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡም አስታውቀዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2024 በጸደቀው "የወደፊት ስምምነት" ላይ የጸጥታው ምክር ቤት መዋቅራዊ የማሻሻያ እርምጃ ለመወሰድ የተቀመጠው አቅጣጫ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቀጣናዊ ፎረም በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Mar 1, 2026 163
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ እያሳደረ ባለው ከፍተኛ ተጽእኖ ምክንያት የቀጣናው የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እና የዜጎች የኑሮ መሰረት አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብ ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል።
የኢጋድ እና ተመድ ትብብር ለቀጣናዊ ሰላም
Feb 26, 2026 194
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት ያላቸውን የጋራ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የኢጋድ የደቡብ ሱዳን ልዩ ልዑክ አምባሳደር ሙሳ ጃማ አሊ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ጉዋንግ ኮንግ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። ልዩ ልዑኮቹ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት በተለይም በደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። በቅርቡ የአፍሪካ ህብረት የአምስት አባል ሀገራት ኮሚቴ (AU C5) እና ኢጋድ ያደረጉት የጋራ ጉባኤ የተገኙ ውጤቶች ላይም መክረዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ሰላም፣ መረጋጋት እና ቀጣናዊ ትብብር እውን እንዲሆን ያላቸውን ቅንጅት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደሆኑ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ
Mar 2, 2026 201
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል። የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 258
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።
የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 269
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን። የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው። የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል። የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት። የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 710
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 293
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮ-እስራኤል ታሪካዊ ትስስር
Feb 24, 2026 395
(በአየለ ያረጋል) ጥልቅ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው፤ ኢትዮጵያና እስራኤል። የሁለቱ ሃገራት ዘመናትን የተሻገረው ግንኙነት አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች የተጠናከረ ሆኖ ይገኛል። የሀገራቱ ግንኙነት ግን እንደየስርዓተ መንግስታቱ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባህሪ መልኩን እየለዋወጠ እና ውጣ ውረዶችን እያለፈ የተሻገረና ጠንካራ መሆኑም ይታወቃል። የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳክ ሄርዞግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ የሃገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጠቅሰው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እና የእስራኤል ግንኙነት ታሪካዊ ገጽታ፦ ሃገራቱ የግንኙነታቸው ትርክት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በንግሥተ ሳባ እና በንጉሥ ሰለሞን ዘመነ መንግስት እንደሆነ አፈ ታሪክ ያስረዳል። ይህ አፈ-ታሪካዊ እርሾ ከኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ስርወ መንግስት ጋርም ቀጥሏል። በመካከለኛው እና በዘመነ መሳፍንት ዘመን ሃይማኖትና ንግድ ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ አስተሳስሯል። በተለይም ዴር ሱልጣንን ጨምሮ በኢየሩሳሌም የሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት መኖር የሁለቱን ሀገራት ባህላዊ ተጋምዶሽ አጎልብቷል። ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ከእስራኤል ሀገረ መንግስት ዳግም መመስረት በኋላም በዘመናዊት ኢትዮጰያ ታሪክም ቀጥሏል። የኢትዮ እስራኤል ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ፦ የዘመናዊ የኢትዮ-እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት የተወጠነው በአውሮፓውያኑ ዘመን ቀመር በ1956 ሲሆን በ1961 ይፋዊ የተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጀምሯል። በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግስት የተጀመረው የሁለቱ ሀገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ወዳጅነት ስትራቴጂካዊ ጥቅምን ያማከለና የወቅቱን የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ የዋጀ ግንኙነት እንዲመሰርቱ አድርጓል። በንጉሳዊ ስርዓተ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ እና ሌሎች የልማት ቴክኒካል ድጋፍ የደረሰ ወዳጅነት ነበራቸው። በደርግ ዘመነ መንግስት ሁለቱ ሀገራት በእስራኤለና አረቦች ጦርነት ሳቢያ መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል። ያም ሆኖ በግልጽም ሆነ የህቡዕ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደነበራቸው ይወሳል። መጀመሪያ ላይ ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በደርግ መንግስት መጨረሻ ዓመታት (በአውሮፓውያኑ 1989) የኢትዮ-እስራኤል ይፋዊ ግንኙነት ዳግም ተጀምሯል። የ"ኦፕሬሽን ሙሴ" (1984) እና "ኦፕሬሽን ሰለሞን" (1991) የተሰኙ ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል የማጓጓዝ ተልዕኮዎችም በሁለቱ ሀገራት መንግስታት ስምምነት የተካሄዱ መሆናቸውን ልብ ይሏል። በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (ከ1983 ዓ.ም) ጀምሮ ደግሞ የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሟላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጥሏል። በፈረንጆቹ 1992 ኢትዮጵያ በእስራኤል ኤምባሲዋን ከፍታለች። በፈረንጆቹ 2003 ኢትዮጵያና እስራኤል የኢንቨስትመቶች ማስፋፊያና ጥበቃ ስምምነት ተፈራርመዋል። በ1996 ዓ.ም (እ.ኤ.አ 2004) የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አሪኤል ሻሮን ጋር ያደረጉት ታሪካዊ ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሳድጎታል። ጉብኝቱን ተከትሎ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ያጠናከሩ የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገዋል። በተለይም በቴክኖሎጂና ግብርና ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ከፍ ብሏል። በአፍሪካ ቀንድ ደህንነትና ፀረ ሽብር ጉዳዮች እንዲሁም በወታደራዊ ስልጠና፣ የደህንነት መረጃ ልውውጥና የድንበር ጥበቃ ቴክኖሎጂ በትብብር ለመስራት መሰረት ጥለዋል። በአውሮፓውያን አቆጣጠር 2016 ደግሞ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋርም መክረዋል። በተመሳሳይ በፈረንጆቹ በ2017 የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እስራኤልን ጎብኝተዋል። ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በየራሳቸው ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ በትብብር ቆመዋል። በዓለም አቀፍ መድረኮች አንዳቸው ለሌላው ድምጽ በመስጠት ተደጋግፈዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ጨምሮ ኢትዮጵያ ለብሔረታዊ ጥቅሞቿ መጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እስራኤል አሉታዊ ምላሽ አልሰጠችም። ይልቁንም እስራኤል ኢትዮጵያን ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ ሁነኛ በር አድርጋ ትቆጥራለች። ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮ-አስራኤል ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴካዊ አጋርነት አድጓል። በ2011 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በእስራኤል ያደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ደግሞ የሀገራቱ የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ እንዲታደስ አስችሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ታሪካዊ የተሰኘውን ምክክር አድረገዋል። መሪዎቹ በሰጡት ገለጻም በአምስት ነጥቦች ላይ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ስምምነቶችን በኢኮኖሚ፣ በግብርና፣ በውሃ፣ በመስኖ፣ በጤና እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መፈራረማቸውን አውስተው ነበር። በግብርና፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በጸጥታ ዘርፎች ላይ አብሮ ለመስራት ተስማምተው እንደነበርም እንዲሁ። ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ፦ ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስራቸውን ወደ ልማት በመለወጥ የንግድና ኢንቨስመንት ግንኙነታቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አከናውነዋል። የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እየጎለበተ መጥቷል። ለአብነትም የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመናዊ ግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ተሰማርተዋል። በማዕድን ዘርፍ (በፖታሽ)፣ በማምረቻ ዘርፍ( በጨርቃጨርቅ እና በኬሚካል ኢንዱስትሪዎች) እንዲሁም በጤናና ፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ ነው። በተለይም በግሪን ሃውስ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ፣ በማምረቻ እና በፋርማሲዩቲካል (የመድኃኒት) ዘርፎች ሁነኛ ተሳትፎ አድርገዋል። በተመሳሳይ በንግድ ልውውጥ ረገድ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሰሊጥና ሌሎች የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ወደ እስራኤል በስፋት ትልካለች። በአንጻሩ እስራኤል የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የግብርና ግብዓቶችን (ማዳበሪያና ኬሚካሎች)፣ የሕክምና መሣሪያዎችን እና የደህንነት ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ታቀርባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ በደረቅ አካባቢ ግብርና ስመጥር የሆነችው እስራኤል በዘርፉ የኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት አጋር ስትሆን በዘመናዊ መስኖ፣ የአቮካዶና የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ እና የወተት ምርታማነት አጋዥ ቴክኖሎጂዎች በጎ ተሳትፎ ታደርጋለች። በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ወዳጅነት መጠናከር ቤተ-እስራኤላውያን እንደ ድልድይ አገልግለዋል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከ160 ሺህ በላይ መሰረታቸው ከኢትዮጵያ የሆኑ እስራኤላዊያን ዜጎች አሉ። እነዚህ ዜጎች ለኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲ ሁነኛ ድልድይ ሆነዋል። በተለይም በእስራኤል የሰለጠኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ በማስቻል በዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በንግድ ስራ ረገድ ውጤታማ ግንኙነት እንዲፈጠር መልካም አጋጣሚ ፈጥጠሯል። ይህም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያቸውን ከፍ አድርጎታል። የፕሬዝዳንት ሔርዞግ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ መምጣት የሁለቱን ሃገራት የጸና ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ የሚያጎለብት እንደሚሆን ይጠበቃል። በአህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም በጋራ የሚያከናውኑትን ስራ የሚያጠናክሩበት ምቹ ሁኔታም ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1131
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 1117
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3613
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2413
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8209
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6692
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 403
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ። እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል። የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል። በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል። ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል። በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት
Feb 26, 2026 380
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ ጀምረዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ ነው። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ ያደርሰዋል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት አዘርባጃን እ.አ.አ በ1991 ነጻነቷን ማግኘቷን ተከትሎ ነው። የሀገራቱ ግንኙነት ከእ.አ.አ 1990ዎች መግቢያ አንስቶ እያደገ መጥቷል። አዘርባጃን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ኤምባሲ የከፈተች ሲሆን ይህም የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ትብብር እንዲጠናከር በር ከፍቷል። በቱርክዬ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ከአዘርባጃን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስራ የሚሸፍን ሲሆን ፖለቲካ፣ ትምህርት እና ባህል ሀገራቱ ካላቸው የትብብር መስኮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ከሚያመላክቱ ጉዳዮች መካከል በባለብዙ ወገን መድረክ በገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) መድረክ በትብብር እየሰሩ መገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2019 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 18ኛው የገለልተኛ ሃገራት ንቅናቄ (ናም) ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች። የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ 120 አባል ሃገራትን ያቀፈና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓለም ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው። የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ወዳጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። በሀገራቱ መካከል ተከታታይ የሆኑ የባህል ልውውጥ መድረኮች ተካሄደዋል። ለዚህም እ.አ.አ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች በአዘርባጃን የትምህርት እድል አግኝተው ይከታተሉ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ከኢኮኖሚ አንጻር እ.አ.አ በ2017 በአዘርባጃን የተካሄደው የሁለቱ ሀገራት የቢዝነስ ፎረም ተጠቃሽ ነው። በወቅቱ ጨርቃጨርቅን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ ሀገራቱ እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ልውውጥ ምጣኔ ለማሳደግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ባለስልጣናት መካከል የሚደረጉ የጉብኝት ልውውጦች እያደጉ መጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በግንቦት ወር 2016 ዓ.ም በአዘርባጃን ጉብኝት ማድረጋቸወ ይታወሳል። ኢትዮጵያና አዘርባጃን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማሳደግና በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም እንዲሁ። ምክክሩ እጅግ ውጤታማ የነበረ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝብ ዕድገት እና ብልፅግና በመደጋገፍና በትብብር መንፈስ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውም በወቅቱ ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአዘርባጃን የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትር ኮሎኔል-ጀነራል ኢይቫዞቭ ቪላያት ሱለይማን ጋር በነበራቸው ውይይት የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ የኢትዮጵያን እና አዘርባጃን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብሮችን ማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ስራዎች ላይ መክረዋል። በውይይቱም በመረጃ፣ በፀጥታና ደህንነት ዘርፎች የጋራ ትብብር አቅም ግንባታና ሌሎች ጉዳዮች ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመፈጸም መስማማታቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸው ይታወሳል። እ.አ.አ በ2017 በወቅቱ የአዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኤልማር ማማድያሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውና የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በቋሚነት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። የአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ማኅበራዊ ፈጠራ ተቋም ሊቀ መንበር ኦልቪ ሜዲዬቭ የብሔራዊ ቤተመንግሥት እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል። ኦልቪ ሜዲዬቭ በወቅቱ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተወያይተዋል። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያልቺን ራፊየቭ የተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን የምትልካቸው ምርቶች ብዝኀነትን ለማሳደግና ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አዘርባጃን ከምትልካቸው ምርቶች መካከል ሰሊጥ፣ የተቆላ ቡና፣ ተልባ፣ የፍየል እና የበግ ሥጋን ጨምሮ ሌሎች ምርቶች እንደሚገኙበት ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ በአዘርባጃን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ቩጋር ሙስታፋይ የተመራ ልዑክ በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ከመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው ይታወሳል። በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ንግድ ትብብር ላይ ያተኮረው ሶስተኛ የኢትዮ-አዘርባጃን የውይይት መድረክ በጥር ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ከውይይቱ በኋላ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግና ተጨማሪ እድሎችን መፈተሽ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ ደርሰዋል። 29ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 29) በህዳር ወር 2017 ዓ.ም በአዘርባጃን መካሄዱ ይታወቃል። በጉባኤው ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተመራ ልዑክ ተሳትፎ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑክ ከአዘርባጃን ባለስልጣናት ጋር በመወያየት ሀገራቱ በአካባቢ ጥበቃ፣ አየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አረንጓዴ ልማት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በሀገራቱ መካከል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተደረጉ ውይይቶችና የልምድ ልውውጦች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር እየጠነከረ መምጣቱን ያሳያል። ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ግብርና፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ትምህርት እና ባህልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን ለማጠናከር ይሻሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአዘርባጃን ሪፐብሊክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማድረግ መጀመራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የኢትዮጵያ እና የአዘርባጃን ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለዚህም ጉልህ ማሳያው በጠንካራ ትብብር የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጎልቶ እንደሚታይ አንስቷል። የዛሬው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ጉብኝትም የዚሁ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ማሳያ መሆኑን ጠቁሟል። ይህ ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የላቀ እና ትርጉም ያለው ደረጃ እንደሚያደርስ ይጠበቃል ሲልም ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጉብኝት በመሪ ደረጃ የሚደረግ መሆኑ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ትርጉም ይሰጠዋል። ሶስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አዘርባጃን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚሸጋገር የቅርብ ዓመታት ውይይቶች እና ጉብኝቶች ማሳያ ናቸው።