ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በሲዳማ ክልል ጤናማ የንግድ ሥርዓትን በመፍጠር የዋጋ ንረትን የመከላከሉ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 19, 2025 41
ሀዋሳ ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ጤናማ የንግድ ሥርዓት በመፍጠር የኑሮ ውድነት ጫናን የሚያቃልሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመላከተ፡፡ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የሕገ ወጥ ንግድ፣ ኮንትሮባንድና፣ የገበያ ንረት መከላከል የጋራ ግብረ ኃይል የንቅናቄ መድረክ አካሄዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የትምህርት ቢሮ ኃላፊና የግብረ ኃይሉ ሰብሳቢ አቶ በየነ በራሳ በክልሉ ጤናማ የንግድ ሥርዓትን በመፍጠር የኑሮ ውድነት ጫናን የማቃለል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል፡፡ በክልሉ የምርቶች ነፃ ዝውውር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደሩ የሚገኙ ያልተፈቀዱ ኬላዎች የሚነሱ መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡ ለዚሁ ተግባር የተቋቋመው ግብረ ኃይልም በዚህ ረገድ ተቀናጅቶ በመስራት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት መወጣት እንዳለበትም ጠቁመዋል፡፡ የክልልና የፌዴራል ተቋማትን በቅንጅት ያቀፈው ግብረ ኃይሉ ባለፈው ዓመት ሕገወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎችንና የኮንትሮባንድ ንግድን የመከላከል ስራ ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሠላማዊት መኩሪያ ናቸው ፡፡ ቢሮው ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከጉምሩክ ኮሚሽን ሀዋሳ ቅርንጫፍ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ባደረገው የመከላከል ሥራ ከ145 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት የያዘ ሲሆን ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ እጃቸው ያለባቸውን አካላት በህግ ተጠያቂ የማድረግ ስራ መስራቱን አስረድተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በተለይ የነዳጅ ግብይቱን ሕጋዊነት ለመጠበቅ ብሎም በዕጥረት ምክንያት በህብረተሰቡ ላይ የሚከሰቱ ጫናዎችን ለማቃለል በየደረጃው በተቀናጀ መንገድ ስንሰራ ቆይተናል ብለዋል፡፡ ከነዳጅ ሕገወጥ ዝውውርና ንግድ ጋር በተያያዘ በ11 ማደያዎችና በ14 ሕገወጥ ነዳጅ ቸርቻሪዎች ላይ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ጠቁመው ከ70 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ በሕገወጥ መልኩ ሲዘዋወር መያዙን ገልፀዋል፡፡ በቡና፣ በሸቀጦችና በሌሎች ምርቶች ላይም እንዲሁ ጠንካራ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን የገለፁት ኃላፊዋ ያለፈው ዓመት ጉድለቶቻችንን በመገምገም በተያዘው በጀት ዓመት ይበልጥ የተጠናከረ የጋራ ሥራ እንሰራለን ብለዋል ፡፡ ባለፈው ዓመት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅተን በመስራታችን ውጤት ማምጣት ብንችልም ከችግሩ ስፋት አኳያ ብዙ ልንሰራቸው የሚገቡ ሥራዎች አሉ ያሉት ደግሞ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተስፋዬ ዴቢሶ ናቸው፡፡ ህብረተሰቡ ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን ለመከላከልና ለሕግ መከበር እየሰጠ ያለው ቀና ምላሽ የሚበረታታ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ ወንጀሎችን ህዝቡን በማሳተፍ በትኩረት ልንከላከላቸው ይገባል ብለዋል፡፡ በንቅናቄ መድረኩ ላይ የክልልና የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የፀጥታ አካላት እንዲሁም የዞን፣ የከተማ አስተዳደርና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በክልሉ በተቋማት መልሶ ግንባታ ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት መስጠት ተችሏል
Oct 19, 2025 33
ኮምቦልቻ ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በተለያዩ ዘርፎች መልሰው እንዲቋቋሙ በተደረጉ ተቋማት ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት መስጠት መቻሉን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር የሚያከናውነውን የመልሶ ማቋቋም ተግባር በኮምቦልቻ ከተማ ገምግሟል። የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን እንደገለጹት፣ በክልሉ በተለያየ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ተቋማትን በተሻለ ሁኔታ መልሶ የማቋቋም ስራ እየተከናወነ ነው። በክልሉ በጀት፣ በተለያዩ የልማት ድርጅቶችና አጋር አካላት ትብብር የመልሶ ማቋቋም ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም በርካታ የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃ፣ የግብርና፣ አስተዳደርና ሌሎችም ማህበራዊ ተቋማት በተሻለ ደረጃ መልሰው ተገንብተውና ተቋቁመው የተሻለ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል። የመልሶ ማደራጀት ስራው በሰላም እሴት ግንባታ እንዲሁም በሥራ እድል ፈጠራና ሌሎች ዘርፎችንም ውጤታማ ለማድረግ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። ሕብረተሰቡ አንድነቱንና ሰላሙን በማስቀጠል ተቋማትን መጠበቅና ለሕዝብ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ እንዳለበት አመልክተዋል። የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱ ሙሄ በበኩላቸው፣ በተለያየ ምክንያት የተጎዱ የውሃ፣ የትምህርት፣ የጤናና ሌሎችም ተቋማትን በተሻለ ሁኔታ መልሶ በማቋቋም ለሕብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እየተደረገ ነው ብለዋል። በዚህም በርካታ የመሰረተ ልማት ተቋማት በአዲስ መልክ ተገንብተው ጭምር ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። በሰሜን ሽዋ ዞን የቀወት ወረዳ ገንዘብ ጽህፈት ቤት የፕሮጀክት ክትትልና ድጋፍ ባለሙያ አቶ አሸናፊ ጌታቸው በዞኑ በተለያየ ምክንያት የተጎዱ ተቋማት በተሻለ ደረጃ ተገንብተው ለሕብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የፃግብጂ ወረዳ ገንዘብ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ንጉስ ሙሉጌታ በበኩላቸው የተለያዩ ተቋማትን ደረጃ በማሻሻል ሕብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት ማግኘት ችሏል ብለዋል። በግምገማ መድረኩ የክልል፣ የዞንና ወረዳ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የአርባ ምንጭ የዓዞ እርባታን ለማዘመን የሚያስችል የ50 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክት ተቀርጾ ወደ ተግባር ተገብቷል
Oct 19, 2025 36
አርባምንጭ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የአርባ ምንጭ የዓዞ እርባታን ለማዘመን የሚያስችል የ50 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክት ተቀርጾ ወደ ተግባር መገባቱን የጋሞ ልማት ማህበር አስታወቀ። ማህበሩ በያዝነው በጀት ዓመት ከቱሪዝም እና ከቆዳ ሽያጭ እስከ 20 ሚሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት አቅዶ እየሠራ መሆኑም ተመላክቷል። የቱሪዝም አገልግሎት፣ የብዝሃ ሀብት ጥበቃ፣ የምርምርና የስራ ዕድል ፈጠራን ዓላማ በማድረግ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የአርባ ምንጭ የዓዞ ራንች የተመሰረተው በ1976 ዓ.ም ነው። ለ30 ዓመታት በመንግስት ሲተዳደር የቆየውን የዓዞ እርባታ (ራንች) የጋሞ ልማት ማህበር ተረክቦ ማስተዳደር ከጀመረ አንድ ዓመት የሆነው ሲሆን ማህበሩ ራንቹን ለማዘመን መጠነ ሰፊ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል። የጋሞ ልማት ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዋኖ ዋሎሌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ማህበሩ የዓዞ ቆዳ እና የቆዳ ውጤቶች ግብይት እንዲሁም የቱሪዝም ገቢ አቅምን ለማሳደግ የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎችን እያከናወነ ነው። የዓዞ እርባታው ሰፊ ቁጥር ያለው ዓዞ መያዝ እንዲችል ገንዳዎችን ማስፋፋትና ለቱሪስት ሳቢ እና ማራኪ ማድረግ ከስራዎቹ መካከል መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ቱሪስቶቹ በቆይታቸው የምግብና የመጠጥ አገልግሎቶችን የሚያገኙበት መናፈሻዎችን ለመገንባት እንዲሁም የዓዞ ቆዳ ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን አስረድተዋል። ከዚህ ቀደም ጎብኚዎች ዓዞዎችን ብቻ ሲጎበኙ እንደነበር ጠቁመው በአዲሱ ማሻሻያም ከዚህ በፊት ያልነበሩ እንደ ዘንዶ፣ ጥንቸል፣ ኤሊ እና ሌሎች እንስሳትን በማምጣት የቱሪዝም ዘርፉን ገቢን ለማሳደግ በስፋት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በጋሞ ልማት ማህበር የአርባ ምንጭ ዓዞ ራንች ኃላፊ ተወካይና አስጎብኚ አቶ አስደሳች ዳንኤል በበኩላቸው የዓዞ እርባታውን ዘመናዊ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ በመሆናቸው ሰፊ ለውጦች እየታዩ ነው ብለዋል። በዓዞ እርባታው በአሁኑ ወቅት ከ4 ሺህ በላይ ዓዞዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ከእነዚህ መካከል ከ2 ሺህ 700 የሚልቁት ለቆዳ ሽያጭ የደረሱ መሆናቸውን አስረድተዋል። በአርባ ምንጭ የዓዞ እርባታ ጉብኝት ሲያደርጉ ያገኘናቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪው አቶ ሽመልስ አረጋ ዓዞን ከዚህ ቀደም በፎቶ እና በቪዲዮ ብቻ ማየታቸውን ጠቅሰው ዓዞን በአካል ለማየት በመቻላቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። በዓዞ እርባታው የተጀመሩ የማሻሻያ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ጠቅሰው ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ያሉ የቱሪስት ፀጋዎችን መመልከትና ማወቅ እንዳለባቸውም አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ወንዞችና ቀይ ባሕር የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልጽግና የሚበይኑ ናቸው
Oct 19, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 9/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ወንዞችና ቀይ ባሕር የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልጽግና የሚበይኑ መሆናቸውን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ሳዲቅ አደም ገለጹ። በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በኢፌዴሪ መከላከያ ዋር ኮሌጅና በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትብብር "የሁለቱ የውሃ ሥርዓቶችና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ነፃነት፥ የዓባይና የቀይ ባሕር ትስስር እና የአፋር ክልልን ስትራቴጂካዊ ሚና መዳሰስ" በሚል መሪ ሃሳብ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ምክክር ተካሂዷል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ሳዲቅ አደም፥ የዓባይ ወንዝና ቀይ ባሕር የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልጽግና የሚበይኑ ወሳኝ ወንዞች ናቸው ብለዋል። በዚህም በዓባይ ወንዝ ላይ የሙሉ ጊዜ መረጃ የሚያስተጋቡ ኃይሎች ኢትዮጵያን በቀይ ባሕር ጉዳይ አትናገሪ የማለት ምክንያትና መብት እንደሌላቸው ገልጸዋል። እኛ ኢትዮጵያውያን በዓባይ ወንዝ ላይ የነበረንን ቁዘማ ህዳሴ ግድብን በመገንባት መስበር ችለናል ሲሉም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያን የቀይ ባሕር ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ የተጀመረውን ጥረት ሁሉም ዜጋ የጋራ አጀንዳ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። በትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር የፖሊሲና ስትራቴጂ ተመራማሪ ተመስገን ዋለልኝ(ዶ/ር)፥ አስተማማኝ የባሕር በር ማጣታችን በሎጀስቲክስና በትራንስፖርት ዘርፍ ውድ ዋጋ እያስከፈለን ነው ብለዋል። ይህም በወጪና ገቢ የንግድ ሥርዓት ላይ ጫና በማሳደር ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዳንሆን ከማድረጉ ባለፈ የኢኮኖሚ ዕድገታችን በሚፈለገው መልኩ እንዳይጓዝ እንቅፋት ሆኗልም ነው ያሉት። ኢትዮጵያውያን የባሕር በር መዳረሻ አለመኖር የሚያደርሰውን ተፅዕኖ በመገንዘብ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ በትብብር መስራት አለብን ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ተባባሪ ተመራማሪ ብሌን ማሞ፥ የባሕር በር ባለቤትነት ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ካለው ፋይዳ ባሻገር ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚፈጥረውን ዕድል ማየት እንደሚገባ ተናግረዋል። ቀጣናዊ የሰላምና መረጋጋት የኃይል ሚዛንን ለማስጠበቅም የኢትዮጵያን የባሕር ኃይልና የመከላከያ ሠራዊት በአስተማማኝ መሠረት መገንባት እንደሚያስፈልግም አጽነኦት ሰጥተዋል። የዓለም አቀፍ የህግ ተመራማሪው ደጀኔ የማነ፥ የመንግስታቱ ድርጅት ኢትዮጵያና ኤርትራን በኮንፌዴሬሽን ሲያዋህድ በርካታ ሀገራት የኢትዮጵያን ታሪካዊና ተፈጥሯዊ የባሕር በር እና የወደብ ባለቤትነት እንዲካተት አድርገዋል ብለዋል። የ2010 የኢትዮ-ኤርትራ ድንበር ኮሚሽን ውሳኔዎችና አጠቃላይ ሂደቶችን ታሳቢ በማድረግም በዓለም አቀፍ ሕግ ክርክር የማድረግ ዕድል እንዳላት አስረድተዋል።
የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና አህጉራዊ የገበያ መዳረሻዎችን በማስፋት የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ አለው
Oct 19, 2025 68
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጣና በመታገዝ ምርቶቿን ለአፍሪካ ገበያ ማቅረብ መጀመሯ አህጉራዊ የገበያ መዳረሻዎችን በማስፋት የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። የአገር ውስጥ አምራቾች በስምምነቱ በመታገዝ ምርታቸውን በጥራት ለገበያ በማቅረብ ተወዳዳሪነታቸውን ማጉላት እንደሚጠበቅባቸውም ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር የሰው ሃብት ልማትና ድህነት ቅነሳ ከፍተኛ ተመራማሪ ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የህዝብ ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ አገራት የተሻለ የገበያ እድል አላቸው። በዚህ ዕድል ለመጠቀም ከጎረቤት አገራት ጋር ኢኮኖሚያዊ ትስስር መፍጠር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው አብራርተዋል። የተፈጠረው ዕድል የገበያ ተደራሽነትን ለማስፋትና ምርትን በብዛት ለማቅረብ አይነተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመው፤ አምራቾች በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ምርት እንዲያቀርቡ ያስችላቸዋል ብለዋል። በተጨማሪም ከተለያዩ አገራት ጋር የገበያ ስርዓት ልምድ ልውውጥ ለማድረግ፣ የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ለመፍጠርና የኢኮኖሚ ስርአቱን ለማቀናጀት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው አንስተዋል። ኢትዮጵያ በአህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጣና በመታገዝ ምርቶቿን ለአፍሪካ ገበያ ማቅረብ መጀመሯ ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ መጎልበት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ነው ተመራማሪው ያስረዱት። በኢትዮጵያ የኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቡድን መሪና ከፍተኛ ተመራማሪ መዚድ ናስር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና፣ አባል አገራት በታሪፍ ስምምነት እንዲገበያዩ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በተጨማሪም የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማጉላት ለአገር ውስጥ አምራቾች የገበያ እድልና ትስስር ለመፍጠር፣ የተለያዩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባትና አማራጭ የገበያ እድል ለመፍጠር አይነተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። የተዘረጋው ስርዓት አገራት በኢኮኖሚ እንዲተሳሰሩ ከማድረግ ባሻገር ማህበራዊና ፖለቲካዊ ፋይዳው ጉልህ መሆኑን አስረድተዋል። ዓለም አቀፋ የንግድ ስርዓት በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ስምምነቱ ተግባራዊ መደረጉ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ለማጠናከር የሚያግዝ ነው ብለዋል። የአገር ውስጥ አምራቾች ምርቶቻቸውን በላቀ ጥራት በማቅረብ ተወዳዳሪነታቸውን ማጉላት እንደሚጠበቅባቸው ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) አስገንዘበዋል። መዚድ ናስር (ዶ/ር) በበኩላቸው አምራቾች ምርቶቻቸውን የሚልኩባቸውን አገራት ፍላጎትና አለም አቀፍ የግብይት ስርአትን በሚገባ መረዳት አለባቸው ብለዋል። በቴክኖሎጂ የታገዘ የአሰራር ስርአት ተግባራዊ ማድረግ እንዲሁም ዲዛይንና ጥራትን በሚመለከት የተሻለ ግንዛቤ ማዳበር ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል ሲሉ ምሁራኑ አሳስበዋል።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ ነው
Oct 19, 2025 86
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 9/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ እንደሚገኝ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የብሪክስ ሴክሬታሪያት ዳይሬክተርና የቀድሞው በኤርትራ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት ዘርይሁን መገርሳ ገለጹ። በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ዋር ኮሌጅና በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትብብር የሁለቱ የውሃ ሥርዓቶችና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ነፃነት፥ የዓባይና የቀይ ባሕር ትስስር እና የአፋር ክልልን ስትራቴጂካዊ ሚና መዳሰስ" በሚል መሪ ሃሳብ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ምክክር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ የዓባይ ቀይ ባሕር የስትራቴጂ መሠረት የጂኦ-ስትራቴጂክ ደረጃ ትንተና ጉዳዮችን የሚያትት የመነሻ ጽሁፍ ቀርቦ ምክክር ተደርጎበታል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የብሪክስ ሴክሬታሪያት ዳይሬክተርና የቀድሞው በኤርትራ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት ዘርይሁን መገርሳ፥ ታላቁ የህዳሴ ግድብና የቀይ ባሕር ጉዳይ ከፊት የተሰለፉ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ ነው ብለዋል። በዚህም ኢትዮጵያ ህዳሴን በማጠናቀቅ ስጋትን በድል ቋጭታለች ያሉት ዲፕሎማቱ፥ የኢትዮጵያን ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ፣ ጂኦግራፊያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዓለም አቀፍ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ(ዶ/ር፥ ዓለም አቀፍ የውሃ ሃብቶች ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ወሳኝ ናቸው ብለዋል። የኢትዮጵያን ፍትሕዊ የባሕር በር ጥያቄ በዓለም አቀፍና አሕጉር አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ ማስመዝገብ ተችሏል ሲሉም ገልጸዋል። የባሕር መዳረሻ ሳይኖራት ኢትዮጵያ የህዝቦቿን ዘላቂ ልማትና ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ አዳጋች መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን የባለቤትነት ጥያቄም ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት ማሰሪያ ገመድ እንደሆነ አስረድተዋል። በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር ጋሻው አይፈራም(ዶ/ር)፥ የሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የኃይል ሚዛንን ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝና ቀይ ባሕር ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ደኅንነትና ብልፅግናም በቀጥታ ከሁለቱ የዓባይና ቀይ ባህር ውሃዎች ጋር የተቆራኘ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ደኅንነት ከሁለቱ የዓባይና የቀይ ባሕር የውሃ አካላት ጋር የማይነጣጠል የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ እንደሆነም አስገንዝበዋል። በኢፌዴሪ ዋር ኮሌጅ የሥልጠናና ትምህርት ዲንና ምክትል ኮማንደንት ብርጋዴር ጄኔራል ጥላሁን ደምሴ፥ የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ለማረጋገጥ ዜጎች በስትራቴጂ የተደገፈ ግንዛቤ እንዲያገኙ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። ኢትዮጵያውያንም በህዳሴ ግድብ ስኬት የሳዩትን ሁለንተናዊ ትብብር የባሕር በር ባለቤትነትን ምላሽ ለማሰጠት በሚደረገው ጥራት በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። በኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ ጥላሁን ተፈራ (ዶ/ር)፥ የቅኝ ግዛት ዘመን ስምምነቶች የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ምክንያታዊ ያደርገዋል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው ውጤታማ አመራር የህዝቡን ተጠቃሚነት ከፍ ያደረጉ ስራዎች እንዲከናወኑ አስችሏል
Oct 19, 2025 122
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው ውጤታማ አመራር የህዝቡን ተጠቃሚነት ከፍ ያደረጉ ስኬታማ ስራዎች እንዲከናወኑ ማስቻሉን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ሩብ በጀት ዓመት በፓርቲ እና በህዝብ ንቅናቄ ስራዎች ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ እያካሄደ ነው። በመድረኩ የፓርቲው አመራሮች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ በየዘርፉ ያለው አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሀላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፓርቲው ተግባራዊ ያደረገው ውጤታማ አመራር ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬታማ ስራዎች እንዲከናወኑ አስችሏል። ትልልቅ አገራዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች መመረቃቸውን ጠቅሰው፤ በሁሉም መስክ አበረታች ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። መደመርን ማዕከል በማድረግ የፓርቲው፣ የህዝቡና የግሉን ዘርፍ በማቀናጀት ያሉ አገራዊ አቅሞች ጥቅም ላይ እንዲውሉ መደረጉ ለስኬቱ መገኘት ምክንያት ከሆኑ ጉዳዮች መካከል መሆናቸውን ገልጸዋል። ገቢር ነበብ አካሄድን በመከተል በየአካባቢው ያሉ ጸጋዎችን እና ዕድሎችን መሰረት ያደረጉ ተግባራት ተከናውነዋል ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ባህል እየዳበረ መምጣቱን ተናግረዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል። በዛሬው የግምገማ መድረክ በጋራ የታቀዱ ጉዳዮችን አፈጻጸም መገምገም እንዲሁም በቀጣይ ርብርብ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ለይቶ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑን አብራርተዋል። የግምገማ መድረኩ በክልሎች መካከል የልምድ ልውውጥ እንዲኖር በማድረግ የአፈጻጸም ወጥነት እንዲኖር ፋይዳው ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።
የመደመር መንግሥት ስብራቶችን ነቅሶ በማውጣት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ተንትኖ አስቀምጧል - አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር)
Oct 19, 2025 72
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት መጽሐፍ የተጠራቀሙ ችግሮችን እና ስብራቶችን ነቅሶ በማውጣት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ተንትኖ አስቀምጧል አሉ አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር)። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተፃፈው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ዙሪያ በሳኡዲ አረቢያ ሪያድ የኢፌዲሪ ኤምባሲ እና በሪያድ የኢትዮጰያ ኮሙኒቲ ማህበር በጋራ ያዘጋጁት የፓናል ውይይት ተካሄደ። በፕሮግራሙ ላይ በሳኡዲ አረቢያ የኢፌዴሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር) መጽሐፉ እያንዳንዳችንን እንደ ግለሰብ፣ ቤተሰብ፣ ማህበረሰብ እና እንደ ሀገር የሚመለከቱን ጉዳዮች የተካተቱበት ስለሆነ ሁላችንም ሊኖረንና ልናነበው የሚገባ ነው ብለዋል። በተለይም በሀገር ደረጃ የተጠራቀሙ ችግሮችን እና ስብራቶችን ነቅሶ ያወጣ እና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ተንትኖ ያስቀመጠ በመሆኑ ሁላችንም በጥልቀት ልናውቀውና ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። አክለውም በመጽሐፉ ውስጥ ያሉ ሃሳቦች የወደፊት ተስፋዎች ብቻ ሳይሆኑ ባለፉት የለውጥ አመታት ተተግብረው ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ የጀመሩ እና ሀገራችንን ወደተሻለ ብልጽግና ለማሸጋገር ተስፋን የፈነጠቁ መሆናቸውን ገልፀዋል። ይህንንም በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ትልልቅ ፕሮጀክቶች እንዲሁም ከተማውንና ገጠሩን የአገራችንን አካባቢዎች በፍጥነት እየቀየሩ ያሉ ኢኒሼቲቮች ተጀምረው በአጭር ግዜ ውስጥ መጠናቀቅ መጀመራቸው የሃሳቦቹን ተግባራዊነት እና ገቢራዊነት የሚያሳዩ ናቸውም ነው ያሉት። አምባሳደሩ የመጽሐፉ ሽያጭ ገቢ ለሀገር ልማት እና ለበጎ አድራጎት ስራዎች የሚውል መሆኑንም ገልጸዋል። ይህ ደግሞ መፅሐፉ በራሱ እንደ አንድ ራሱን የቻለ ሀገራዊ ፕሮጀክት እንዲታይ የሚያደርገው ነው ሲሉ አንስተዋል። የሪያድ ኮሙኒቲ በተለያዩ ወቅቶች ለሚቀርቡ የሀገር ልማት እና በጎአድራጎት አገራዊ ጥሪዎች ቀናኢነቱን ደጋግሞ እንዳስመሰከረው ሁሉ ይህንን መፅሐፍ ቀድሞ በመውሰድ ግንባር ቀደም ተሳታፊነቱን በማረጋገጡ ታላቅ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። በውይይቱ ላይ መልእክታቸውን ያስተላለፉት በሪያድ የኢትዮጵያውያን ኮሙኒቲ ሊቀመንበር አቶ ሱለይማን ሙሃመድ በበኩላቸው ይህ መጽሐፍ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቤት መገኘት እንዳለበት ተናግረዋል። በመድረኩም የመጽሐፍ ዳሰሳ ውይይት መካሄዱን የኤፍ ኤም ሲ ዘገባ ያመላክታል። በመጨረሻም ለዝግጅቱ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረክቱ አካላት የእውቅና እና የምስክር ወረቀት ሽልማት መርኃ ግብር ተካሂዶ ዝግጅቱ ተጠናቋል። በፕሮግራሙ ላይ አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድርን ጨምሮ ፣ አምባሳደር አወል ወግሪስ ሙሃመድ፣ ዲፕሎማቶች፣ የኮሙኒቲ ሊቀመንበር፣ የተለያዩ የኮሙኒቲ አደረጃጀቶች ፣ መምህራን እና የዳያስፖራ ማህበረሰብ ተሳትፈዋል።
በክልሉ ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶችን በማስረጽ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን የሚከናወኑ ተግባራት ይጠናከራሉ
Oct 18, 2025 126
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶችን በማስረጽ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን ከሚዲያው ጋር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ዛሬ ባካሄደው የሴክተር ጉባኤ ላይ የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ አሸናፊ ኤልያስ እንደገለጹት፤ በክልሉ የልማት ዕቅዶችን ወደተግባር በመቀየር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰራው ሥራ ውጤት እየተገኘ ነው። የልማት ግቦች ወደህዝብ ሰርጸው በእኔነት ስሜት እንዲሳተፍባቸውና ተጨባጭ ውጤት እንዲመጣ ሚዲያው የጎላ ሚና ሲጫወት መቆየቱን አስታውሰዋል። በቀጣይም ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶች ላይ በማትኮር የህዝብን አንድነት ለማጠናከር፣ የልማት ሥራዎችን ለመፋጠንና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ተግቶ መስራት እንደሚገባ ገልጸው፤ ለዚህም ከሚዲያው ጋር በቅንጅት የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። የክልሉ መንግስት ለዘርፉ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ወሰንየለህ ስምኦን፤ ባለፉት ጊዜያት በዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች አተገባበር ላይ ሚዲያን ያሳተፈ ሥራ በመሰራቱ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። ይህም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የልማት ዘርፎች እየተመዘገቡ ላሉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች አቅም እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል። ቢሮው በክልሉ ያሉ የልማት አቅሞች እና ባህላዊ እሴቶች በአግባቡ እንዲተዋወቁና እንዲለሙ እንዲሁም የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ያዕቆብ እንዳሉት፣ ቢሮው በክልሉ ያሉ ጸጋዎችን በመጠቀም የዜጎች የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ እየሰራ ነው። በተለይ ለክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ የተሰጠው ትኩረት በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቅሰው፣ ይህም ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በመድኩ በክልሉ ከሚዲያው ዘርፍ ጋር በተቀናጀ መንገድ በመስራት እየተመዘገበ ላለው ውጤት አበርቶ ላላቸው አካላት ዕውቅና ተሰጥቷል።
ጣና ፎረም ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ ለሚለው መርህ ተግባራዊነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ ነው
Oct 18, 2025 128
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ጣና ፎረም ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ ለሚለው መርህ ተግባራዊነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑ ተገለጸ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሰላምና ደህንነት ጥናት ተቋም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን 11ኛው ጣና ፎረምን ለማካሄድ በተደረጉ ዝግጅቶች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። 11ኛው ጣና ፎረም ከጥቅምት 14 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድም ተገልጿል። ፎረሙ "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እና ባህር ዳር ለሶስት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን፤በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። በፎረሙ ላይ የአፍሪካ አገሮች መሪዎች እና ባለድርሻ አካላት በመገኘት በአፍሪካ የደህንነት ችግሮችና አፍሪካዊ መፍትሔዎች ዙሪያ ልምዳቸውንና እውቀታቸውን የሚያካፍሉበት መርሃ ግብር መዘጋጀቱም ተገልጿል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ 11ኛው የጣና ፎረም በከፍተኛ ደረጃ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል። በአሁኑ ወቅት ዓለም በርካታ ለውጦች እያስተናገደች መሆኑን ገልጸው፤ አፍሪካ ''በምን መልኩ ዕድሎችን ትጠቀማለች? እንዴትስ አትራፊ መሆን ትችላለች?'' የሚለው ርዕሰ ጉዳይ ዋነኛ የፎረሙ ማጠንጠኛ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፎረሙ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ ምክክር የሚደረግበት መርሃ ግብር ያካተተ መሆኑን ገልጸው፤ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች እንደሚወያዩም አብራርተዋል። ጣና ፎረም ለሌሎች አህጉራዊ መድረኮችም እንደ እርሾ ሆኖ አገልግሏል ያሉት ዳይሬክተር ጀነራሉ፤ በፎረሙ እንደመፍትሄ የሚነሱ ሀሳቦች ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ መርህን የተከተለ መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ አኳያ በአፍሪካ አገራት መካከል የጋራ አጀንዳዎች በመቅረጽና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማመላከት አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አስረድተዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሰላምና ደህንነት ጥናት ተቋም ዳይሬክተር ሜርሲ ፍቃዱ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) በበኩላቸው፤ የጣና ፎረም የፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦች እየፈለቁበት መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ ላይ ከአፍሪካ ውጪም ተሳታፊዎችን የሚጋብዝ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም አጋርነት እንዲጠናከር ትልቅ ሚን እየተጫወተ ነው ብለዋል።
በአካባቢያችን ለሚከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን-የምክር ቤት አባላት
Oct 17, 2025 176
ጂንካ፤ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ) :- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመመለስ እየተከናወኑ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የክትትልና ድጋፍ ስራቸውን እንደሚያጠናክሩ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም በጂንካ ከተማ ተካሄዷል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት በአካባቢያቸው እየተከናወኑ ለሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል። የዲላ ሪጂዮ ፖሊሲ ከተማ አስተዳደር ምክትል አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ጂግሶ፤ መንግስት የከተማውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በከተማው የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለስራ ዕድል ፈጠራ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረው የልማት ስራዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድጋፍና ክትትል ተግባራቸውን እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚያሸጋግሩ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ዶቦ አዊኖ ናቸው። የደቡብ ኦሞ ዞን ዝናብ አጠር ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ መሆኑን የገለፁት ምክትል አፈ-ጉባኤዋ፤ አርብቶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ በመስኖ ልማት እንዲሰማራ መንግስት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ የሚተገበሩ የግብርና ልማት ስራዎች የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የአርብቶ አደሩን ኑሮ እየለወጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአሪ ዞን የገሊላ ከተማ አስተዳደር አማካሪ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ታጋይ ፍላቴ፥ በአካባቢው እምቅ የግብርና አቅም እንዳለ ጠቅሰው በአካባቢው ዓመቱን ሙሉ ማልማት የሚያስችል ምቹ የአየር ጠባይ እና በቂ የውሃ ሀብት አለ ብለዋል። እነዚህን አቀናጅቶ በማልማት የአርሶ አደሩን ኑሮ ለመለወጥ እየተሰራ ያለው አበረታች ስራ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በአካባቢው ስንዴና ገብስን የመሳሰሉ ሰብሎች በኩታ ገጠም በስፋት እየለሙ መሆኑን ጠቅሰው፥ ምርቱን ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። በአካባቢው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚያስችሉ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የኮንሶ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ገልገሎ ኦቶማ ናቸው። በዞኑ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ጠቅሰው፥ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ ውጤት ማምጣት መጀመሩን ጠቅሰዋል። በዞኑ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው የህዝቡን አዳጊ ፍላጎት ለማሟላት መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት ከግብ እንዲደርስ ምክር ቤቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው
Oct 17, 2025 181
ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆናቸውን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አመለከተ። የደብረ ብርሃን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13 ዓመት 47ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ መንግስቱ ቤተ እንዳሉት፤ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው። በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፉ ተኪ ምርቶችን በማምረት ገበያን የማረጋጋት ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል። የንግድና ገበያ ማዕከላት ግንባታ ስራዎች ዘመናዊ የግብይት ስርዓት ለመዘርጋት አይነተኛ ሚና እንዳላቸው አንስተዋል። እነዚህና ሌሎች ተግባራት በበጀት ዓመቱ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም በመንግስት ተቋማት የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ መጓደል ችግሮችን በተደራጀ አግባብ በመፍታት ለህዝቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል። የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ግብርን አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ዕቅድ በጥራትና በተደራሽነት መተግበር እንደሚገባም አመልክተዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት፤ ባለፉት ወራት ህብረተሰቡን በማሳተፍ በተከናወኑ የልማትና ሰላምን የማረጋገጥ ተግባራት ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። አሁን ላይም የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ፣ የተቋማትን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም የማሳደግ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም 269 ለሚሆኑ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከመስጠት ባሻገር 18 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማው የተከናወነውን የኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩ በማስፋት ለ1 ሺህ የቤተሰብ መሪዎች ዘመናዊ ቤቶች እንዲገነቡ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። እንዲሁም ሁለት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታና መሰል የልማት ተግባራት በትኩረት ይከናወናሉ ሲሉም አብራርተዋል። ምክር ቤቱ ጉባኤውን በነገው ዕለት እንደሚያጠናቅቅ ታውቋል።
ህግ የማስከበር እርምጃው በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል- አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር)
Oct 17, 2025 202
ገንዳውሃ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል መንግስት የጀመረው ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በምዕራብ ጎንደር ዞን ከገንዳውሃ፣ መተማ ዮሐንስ ከተማና መተማ ወረዳ ከተውጣጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ሰላም ለማምጣት መንግስት ለሰላማዊ አማራጭ ጭምር እድሎችን በማመቻቸት ብዙ መስራቱን አንስተዋል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበልም በጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን በመፍታት ሰላማዊ ሕይወት እየኖሩ መሆኑን ገልጸው ፤ በዘረፋና እገታ ተግባራቸው የቀጠሉ ጽንፈኞች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በመሆኑም በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን መንግስት ሕግ የማስከበር እርምጃውን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል። የመከላከያ ሰራዊት 504ኛ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ሙላው በየነ፤ የመንግስትን የሰላም እድሎች በማይጠቀሙ ፅንፈኞች ላይ ሰራዊቱ ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን አረጋግጠዋል። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ዘረፋና ግድያ በመፈፀም የሕዝብን ሰላም እያናጋ ያለው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የሚወሰደው ሕግ የማስከበር ተግባር ይቀጥላል ብለዋል። የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሁን መንግሥቱ፤ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት በማስጠበቅ ረገድ ማሕበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ የሕግ ማስከበር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚሕ ረገድ የክልሉ ሕዝብ ከጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ያሳየውን ቀና ትብብር አድንቀው በቀጣይም ድጋፉ እንዳይለይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ፤ የዞኑን ሰላም ለመጠበቅ ከፌዴራልና ከክልል ፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሕም በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም መስፈኑን አንስተው፤ የሕዝቡ የሰላም ጥረት መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የግጭትና ጦርነት አዙሪት አብቅቶ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል። ከጦርነት ውድመት እንጂ የሚገኝ ትርፍ አለመኖሩን ሁላችንም እንገነዘባለን ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ፤ ለዘላቂ ሰላም መስፈን የጸጥታ ሃይሉን እናግዛለን ሲሉም አረጋግጠዋል።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ ነው
Oct 19, 2025 86
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 9/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ እንደሚገኝ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የብሪክስ ሴክሬታሪያት ዳይሬክተርና የቀድሞው በኤርትራ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት ዘርይሁን መገርሳ ገለጹ። በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ዋር ኮሌጅና በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትብብር የሁለቱ የውሃ ሥርዓቶችና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ነፃነት፥ የዓባይና የቀይ ባሕር ትስስር እና የአፋር ክልልን ስትራቴጂካዊ ሚና መዳሰስ" በሚል መሪ ሃሳብ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ምክክር ተካሂዷል። የኢትዮጵያ የዓባይ ቀይ ባሕር የስትራቴጂ መሠረት የጂኦ-ስትራቴጂክ ደረጃ ትንተና ጉዳዮችን የሚያትት የመነሻ ጽሁፍ ቀርቦ ምክክር ተደርጎበታል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የብሪክስ ሴክሬታሪያት ዳይሬክተርና የቀድሞው በኤርትራ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት ዘርይሁን መገርሳ፥ ታላቁ የህዳሴ ግድብና የቀይ ባሕር ጉዳይ ከፊት የተሰለፉ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ሰጭነት በመሸጋገር ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ ከፍታ እየተጓዘ ነው ብለዋል። በዚህም ኢትዮጵያ ህዳሴን በማጠናቀቅ ስጋትን በድል ቋጭታለች ያሉት ዲፕሎማቱ፥ የኢትዮጵያን ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ፣ ጂኦግራፊያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዓለም አቀፍ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ(ዶ/ር፥ ዓለም አቀፍ የውሃ ሃብቶች ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ወሳኝ ናቸው ብለዋል። የኢትዮጵያን ፍትሕዊ የባሕር በር ጥያቄ በዓለም አቀፍና አሕጉር አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ ማስመዝገብ ተችሏል ሲሉም ገልጸዋል። የባሕር መዳረሻ ሳይኖራት ኢትዮጵያ የህዝቦቿን ዘላቂ ልማትና ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ አዳጋች መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን የባለቤትነት ጥያቄም ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት ማሰሪያ ገመድ እንደሆነ አስረድተዋል። በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር ጋሻው አይፈራም(ዶ/ር)፥ የሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የኃይል ሚዛንን ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝና ቀይ ባሕር ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ደኅንነትና ብልፅግናም በቀጥታ ከሁለቱ የዓባይና ቀይ ባህር ውሃዎች ጋር የተቆራኘ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ደኅንነት ከሁለቱ የዓባይና የቀይ ባሕር የውሃ አካላት ጋር የማይነጣጠል የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ እንደሆነም አስገንዝበዋል። በኢፌዴሪ ዋር ኮሌጅ የሥልጠናና ትምህርት ዲንና ምክትል ኮማንደንት ብርጋዴር ጄኔራል ጥላሁን ደምሴ፥ የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ለማረጋገጥ ዜጎች በስትራቴጂ የተደገፈ ግንዛቤ እንዲያገኙ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። ኢትዮጵያውያንም በህዳሴ ግድብ ስኬት የሳዩትን ሁለንተናዊ ትብብር የባሕር በር ባለቤትነትን ምላሽ ለማሰጠት በሚደረገው ጥራት በትብብር መስራት እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። በኢፌዴሪ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ ጥላሁን ተፈራ (ዶ/ር)፥ የቅኝ ግዛት ዘመን ስምምነቶች የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ምክንያታዊ ያደርገዋል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው ውጤታማ አመራር የህዝቡን ተጠቃሚነት ከፍ ያደረጉ ስራዎች እንዲከናወኑ አስችሏል
Oct 19, 2025 122
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው ውጤታማ አመራር የህዝቡን ተጠቃሚነት ከፍ ያደረጉ ስኬታማ ስራዎች እንዲከናወኑ ማስቻሉን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ሩብ በጀት ዓመት በፓርቲ እና በህዝብ ንቅናቄ ስራዎች ላይ ያተኮረ የግምገማ መድረክ እያካሄደ ነው። በመድረኩ የፓርቲው አመራሮች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ በየዘርፉ ያለው አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሀላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፓርቲው ተግባራዊ ያደረገው ውጤታማ አመራር ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬታማ ስራዎች እንዲከናወኑ አስችሏል። ትልልቅ አገራዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች መመረቃቸውን ጠቅሰው፤ በሁሉም መስክ አበረታች ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። መደመርን ማዕከል በማድረግ የፓርቲው፣ የህዝቡና የግሉን ዘርፍ በማቀናጀት ያሉ አገራዊ አቅሞች ጥቅም ላይ እንዲውሉ መደረጉ ለስኬቱ መገኘት ምክንያት ከሆኑ ጉዳዮች መካከል መሆናቸውን ገልጸዋል። ገቢር ነበብ አካሄድን በመከተል በየአካባቢው ያሉ ጸጋዎችን እና ዕድሎችን መሰረት ያደረጉ ተግባራት ተከናውነዋል ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ባህል እየዳበረ መምጣቱን ተናግረዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል። በዛሬው የግምገማ መድረክ በጋራ የታቀዱ ጉዳዮችን አፈጻጸም መገምገም እንዲሁም በቀጣይ ርብርብ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ለይቶ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑን አብራርተዋል። የግምገማ መድረኩ በክልሎች መካከል የልምድ ልውውጥ እንዲኖር በማድረግ የአፈጻጸም ወጥነት እንዲኖር ፋይዳው ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።
የመደመር መንግሥት ስብራቶችን ነቅሶ በማውጣት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ተንትኖ አስቀምጧል - አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር)
Oct 19, 2025 72
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር መንግሥት መጽሐፍ የተጠራቀሙ ችግሮችን እና ስብራቶችን ነቅሶ በማውጣት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ተንትኖ አስቀምጧል አሉ አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር)። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተፃፈው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ዙሪያ በሳኡዲ አረቢያ ሪያድ የኢፌዲሪ ኤምባሲ እና በሪያድ የኢትዮጰያ ኮሙኒቲ ማህበር በጋራ ያዘጋጁት የፓናል ውይይት ተካሄደ። በፕሮግራሙ ላይ በሳኡዲ አረቢያ የኢፌዴሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር) መጽሐፉ እያንዳንዳችንን እንደ ግለሰብ፣ ቤተሰብ፣ ማህበረሰብ እና እንደ ሀገር የሚመለከቱን ጉዳዮች የተካተቱበት ስለሆነ ሁላችንም ሊኖረንና ልናነበው የሚገባ ነው ብለዋል። በተለይም በሀገር ደረጃ የተጠራቀሙ ችግሮችን እና ስብራቶችን ነቅሶ ያወጣ እና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ተንትኖ ያስቀመጠ በመሆኑ ሁላችንም በጥልቀት ልናውቀውና ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። አክለውም በመጽሐፉ ውስጥ ያሉ ሃሳቦች የወደፊት ተስፋዎች ብቻ ሳይሆኑ ባለፉት የለውጥ አመታት ተተግብረው ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ የጀመሩ እና ሀገራችንን ወደተሻለ ብልጽግና ለማሸጋገር ተስፋን የፈነጠቁ መሆናቸውን ገልፀዋል። ይህንንም በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ትልልቅ ፕሮጀክቶች እንዲሁም ከተማውንና ገጠሩን የአገራችንን አካባቢዎች በፍጥነት እየቀየሩ ያሉ ኢኒሼቲቮች ተጀምረው በአጭር ግዜ ውስጥ መጠናቀቅ መጀመራቸው የሃሳቦቹን ተግባራዊነት እና ገቢራዊነት የሚያሳዩ ናቸውም ነው ያሉት። አምባሳደሩ የመጽሐፉ ሽያጭ ገቢ ለሀገር ልማት እና ለበጎ አድራጎት ስራዎች የሚውል መሆኑንም ገልጸዋል። ይህ ደግሞ መፅሐፉ በራሱ እንደ አንድ ራሱን የቻለ ሀገራዊ ፕሮጀክት እንዲታይ የሚያደርገው ነው ሲሉ አንስተዋል። የሪያድ ኮሙኒቲ በተለያዩ ወቅቶች ለሚቀርቡ የሀገር ልማት እና በጎአድራጎት አገራዊ ጥሪዎች ቀናኢነቱን ደጋግሞ እንዳስመሰከረው ሁሉ ይህንን መፅሐፍ ቀድሞ በመውሰድ ግንባር ቀደም ተሳታፊነቱን በማረጋገጡ ታላቅ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። በውይይቱ ላይ መልእክታቸውን ያስተላለፉት በሪያድ የኢትዮጵያውያን ኮሙኒቲ ሊቀመንበር አቶ ሱለይማን ሙሃመድ በበኩላቸው ይህ መጽሐፍ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቤት መገኘት እንዳለበት ተናግረዋል። በመድረኩም የመጽሐፍ ዳሰሳ ውይይት መካሄዱን የኤፍ ኤም ሲ ዘገባ ያመላክታል። በመጨረሻም ለዝግጅቱ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረክቱ አካላት የእውቅና እና የምስክር ወረቀት ሽልማት መርኃ ግብር ተካሂዶ ዝግጅቱ ተጠናቋል። በፕሮግራሙ ላይ አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድርን ጨምሮ ፣ አምባሳደር አወል ወግሪስ ሙሃመድ፣ ዲፕሎማቶች፣ የኮሙኒቲ ሊቀመንበር፣ የተለያዩ የኮሙኒቲ አደረጃጀቶች ፣ መምህራን እና የዳያስፖራ ማህበረሰብ ተሳትፈዋል።
በክልሉ ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶችን በማስረጽ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን የሚከናወኑ ተግባራት ይጠናከራሉ
Oct 18, 2025 126
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶችን በማስረጽ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን ከሚዲያው ጋር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ዛሬ ባካሄደው የሴክተር ጉባኤ ላይ የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ አሸናፊ ኤልያስ እንደገለጹት፤ በክልሉ የልማት ዕቅዶችን ወደተግባር በመቀየር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰራው ሥራ ውጤት እየተገኘ ነው። የልማት ግቦች ወደህዝብ ሰርጸው በእኔነት ስሜት እንዲሳተፍባቸውና ተጨባጭ ውጤት እንዲመጣ ሚዲያው የጎላ ሚና ሲጫወት መቆየቱን አስታውሰዋል። በቀጣይም ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶች ላይ በማትኮር የህዝብን አንድነት ለማጠናከር፣ የልማት ሥራዎችን ለመፋጠንና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ተግቶ መስራት እንደሚገባ ገልጸው፤ ለዚህም ከሚዲያው ጋር በቅንጅት የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። የክልሉ መንግስት ለዘርፉ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ወሰንየለህ ስምኦን፤ ባለፉት ጊዜያት በዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች አተገባበር ላይ ሚዲያን ያሳተፈ ሥራ በመሰራቱ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። ይህም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የልማት ዘርፎች እየተመዘገቡ ላሉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች አቅም እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል። ቢሮው በክልሉ ያሉ የልማት አቅሞች እና ባህላዊ እሴቶች በአግባቡ እንዲተዋወቁና እንዲለሙ እንዲሁም የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ያዕቆብ እንዳሉት፣ ቢሮው በክልሉ ያሉ ጸጋዎችን በመጠቀም የዜጎች የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ እየሰራ ነው። በተለይ ለክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ የተሰጠው ትኩረት በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቅሰው፣ ይህም ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በመድኩ በክልሉ ከሚዲያው ዘርፍ ጋር በተቀናጀ መንገድ በመስራት እየተመዘገበ ላለው ውጤት አበርቶ ላላቸው አካላት ዕውቅና ተሰጥቷል።
ጣና ፎረም ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ ለሚለው መርህ ተግባራዊነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ ነው
Oct 18, 2025 128
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ጣና ፎረም ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ ለሚለው መርህ ተግባራዊነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑ ተገለጸ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሰላምና ደህንነት ጥናት ተቋም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን 11ኛው ጣና ፎረምን ለማካሄድ በተደረጉ ዝግጅቶች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። 11ኛው ጣና ፎረም ከጥቅምት 14 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድም ተገልጿል። ፎረሙ "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እና ባህር ዳር ለሶስት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን፤በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። በፎረሙ ላይ የአፍሪካ አገሮች መሪዎች እና ባለድርሻ አካላት በመገኘት በአፍሪካ የደህንነት ችግሮችና አፍሪካዊ መፍትሔዎች ዙሪያ ልምዳቸውንና እውቀታቸውን የሚያካፍሉበት መርሃ ግብር መዘጋጀቱም ተገልጿል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ 11ኛው የጣና ፎረም በከፍተኛ ደረጃ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል። በአሁኑ ወቅት ዓለም በርካታ ለውጦች እያስተናገደች መሆኑን ገልጸው፤ አፍሪካ ''በምን መልኩ ዕድሎችን ትጠቀማለች? እንዴትስ አትራፊ መሆን ትችላለች?'' የሚለው ርዕሰ ጉዳይ ዋነኛ የፎረሙ ማጠንጠኛ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፎረሙ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ ምክክር የሚደረግበት መርሃ ግብር ያካተተ መሆኑን ገልጸው፤ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች እንደሚወያዩም አብራርተዋል። ጣና ፎረም ለሌሎች አህጉራዊ መድረኮችም እንደ እርሾ ሆኖ አገልግሏል ያሉት ዳይሬክተር ጀነራሉ፤ በፎረሙ እንደመፍትሄ የሚነሱ ሀሳቦች ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ መርህን የተከተለ መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ አኳያ በአፍሪካ አገራት መካከል የጋራ አጀንዳዎች በመቅረጽና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማመላከት አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አስረድተዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሰላምና ደህንነት ጥናት ተቋም ዳይሬክተር ሜርሲ ፍቃዱ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) በበኩላቸው፤ የጣና ፎረም የፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦች እየፈለቁበት መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ ላይ ከአፍሪካ ውጪም ተሳታፊዎችን የሚጋብዝ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም አጋርነት እንዲጠናከር ትልቅ ሚን እየተጫወተ ነው ብለዋል።
በአካባቢያችን ለሚከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን-የምክር ቤት አባላት
Oct 17, 2025 176
ጂንካ፤ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ) :- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመመለስ እየተከናወኑ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የክትትልና ድጋፍ ስራቸውን እንደሚያጠናክሩ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም በጂንካ ከተማ ተካሄዷል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት በአካባቢያቸው እየተከናወኑ ለሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል። የዲላ ሪጂዮ ፖሊሲ ከተማ አስተዳደር ምክትል አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ጂግሶ፤ መንግስት የከተማውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በከተማው የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለስራ ዕድል ፈጠራ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረው የልማት ስራዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድጋፍና ክትትል ተግባራቸውን እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚያሸጋግሩ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ዶቦ አዊኖ ናቸው። የደቡብ ኦሞ ዞን ዝናብ አጠር ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ መሆኑን የገለፁት ምክትል አፈ-ጉባኤዋ፤ አርብቶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ በመስኖ ልማት እንዲሰማራ መንግስት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ የሚተገበሩ የግብርና ልማት ስራዎች የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የአርብቶ አደሩን ኑሮ እየለወጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአሪ ዞን የገሊላ ከተማ አስተዳደር አማካሪ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ታጋይ ፍላቴ፥ በአካባቢው እምቅ የግብርና አቅም እንዳለ ጠቅሰው በአካባቢው ዓመቱን ሙሉ ማልማት የሚያስችል ምቹ የአየር ጠባይ እና በቂ የውሃ ሀብት አለ ብለዋል። እነዚህን አቀናጅቶ በማልማት የአርሶ አደሩን ኑሮ ለመለወጥ እየተሰራ ያለው አበረታች ስራ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በአካባቢው ስንዴና ገብስን የመሳሰሉ ሰብሎች በኩታ ገጠም በስፋት እየለሙ መሆኑን ጠቅሰው፥ ምርቱን ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። በአካባቢው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚያስችሉ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የኮንሶ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ገልገሎ ኦቶማ ናቸው። በዞኑ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ጠቅሰው፥ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ ውጤት ማምጣት መጀመሩን ጠቅሰዋል። በዞኑ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው የህዝቡን አዳጊ ፍላጎት ለማሟላት መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት ከግብ እንዲደርስ ምክር ቤቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው
Oct 17, 2025 181
ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆናቸውን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አመለከተ። የደብረ ብርሃን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13 ዓመት 47ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ መንግስቱ ቤተ እንዳሉት፤ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው። በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፉ ተኪ ምርቶችን በማምረት ገበያን የማረጋጋት ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል። የንግድና ገበያ ማዕከላት ግንባታ ስራዎች ዘመናዊ የግብይት ስርዓት ለመዘርጋት አይነተኛ ሚና እንዳላቸው አንስተዋል። እነዚህና ሌሎች ተግባራት በበጀት ዓመቱ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም በመንግስት ተቋማት የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ መጓደል ችግሮችን በተደራጀ አግባብ በመፍታት ለህዝቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል። የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ግብርን አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ዕቅድ በጥራትና በተደራሽነት መተግበር እንደሚገባም አመልክተዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት፤ ባለፉት ወራት ህብረተሰቡን በማሳተፍ በተከናወኑ የልማትና ሰላምን የማረጋገጥ ተግባራት ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። አሁን ላይም የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ፣ የተቋማትን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም የማሳደግ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም 269 ለሚሆኑ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከመስጠት ባሻገር 18 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማው የተከናወነውን የኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩ በማስፋት ለ1 ሺህ የቤተሰብ መሪዎች ዘመናዊ ቤቶች እንዲገነቡ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። እንዲሁም ሁለት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታና መሰል የልማት ተግባራት በትኩረት ይከናወናሉ ሲሉም አብራርተዋል። ምክር ቤቱ ጉባኤውን በነገው ዕለት እንደሚያጠናቅቅ ታውቋል።
ህግ የማስከበር እርምጃው በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል- አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር)
Oct 17, 2025 202
ገንዳውሃ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል መንግስት የጀመረው ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በምዕራብ ጎንደር ዞን ከገንዳውሃ፣ መተማ ዮሐንስ ከተማና መተማ ወረዳ ከተውጣጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ሰላም ለማምጣት መንግስት ለሰላማዊ አማራጭ ጭምር እድሎችን በማመቻቸት ብዙ መስራቱን አንስተዋል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበልም በጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን በመፍታት ሰላማዊ ሕይወት እየኖሩ መሆኑን ገልጸው ፤ በዘረፋና እገታ ተግባራቸው የቀጠሉ ጽንፈኞች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በመሆኑም በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን መንግስት ሕግ የማስከበር እርምጃውን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል። የመከላከያ ሰራዊት 504ኛ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ሙላው በየነ፤ የመንግስትን የሰላም እድሎች በማይጠቀሙ ፅንፈኞች ላይ ሰራዊቱ ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን አረጋግጠዋል። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ዘረፋና ግድያ በመፈፀም የሕዝብን ሰላም እያናጋ ያለው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የሚወሰደው ሕግ የማስከበር ተግባር ይቀጥላል ብለዋል። የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሁን መንግሥቱ፤ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት በማስጠበቅ ረገድ ማሕበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ የሕግ ማስከበር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚሕ ረገድ የክልሉ ሕዝብ ከጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ያሳየውን ቀና ትብብር አድንቀው በቀጣይም ድጋፉ እንዳይለይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ፤ የዞኑን ሰላም ለመጠበቅ ከፌዴራልና ከክልል ፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሕም በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም መስፈኑን አንስተው፤ የሕዝቡ የሰላም ጥረት መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የግጭትና ጦርነት አዙሪት አብቅቶ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል። ከጦርነት ውድመት እንጂ የሚገኝ ትርፍ አለመኖሩን ሁላችንም እንገነዘባለን ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ፤ ለዘላቂ ሰላም መስፈን የጸጥታ ሃይሉን እናግዛለን ሲሉም አረጋግጠዋል።
ማህበራዊ
ትምህርት ቤቶች ዕውቀት በመስጠት ትውልድን ከመገንባት ባለፈ ህይወት በመታደግ ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ ነው
Oct 19, 2025 129
አዳማ ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦ትምህርት ቤቶች ዕውቀት በመስጠት ትውልድን ከመገንባት ባለፈ ህይወት በመታደግ ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ መሆኑ ተገለፀ። የኢትዮጵያ የደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት ዓመታዊ የደም አሰባሰብ ዕቅድ ለማሳካት ከአዲስ አበባ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንና ርዕሰ መምህራን ጋር በአዳማ የጋራ ፎረም እያካሄደ ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ታዬ እንደገለፁት በደም እጦት የሚያልፈውን የዜጎችን ህይወት ለመታደግ በደም አሰባሰብ ሂደት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው። ባለፈው ዓመት ከ423 ሺህ ዩኒት በላይ ደም በመሰብሰብ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎችን ህይወት መታደግ መቻሉን ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ብቻ ከ100 ሺህ በላይ ዩኒት ደም መሰብሰብ መቻሉን የገለፁት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ በዚህም የተማሪዎች፣ የመምህራንና ርዕሰ መምህራን ድርሻ ከፍተኛ ነበር ብለዋል። ትምህርት ቤቶች ዕውቀት በመስጠት ትውልድን ከመገንባት ባለፈ ህይወት በመታደግ ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ጠቁመው በተቋማቱ ያለውን ወጣት ማህበረሰብ በመጠቀም ከአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ለመሰብሰብ የታቀደውን 130 ሺህ ዩኒት ደም ለማሳካት ርብርብ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። በተያዘው በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ 550 ሺህ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ አቅደን እየሰራን ነው ያሉት ምክትል ዳይሬክተሩ በመጀመሪያው ሩብ ዓመትም ከ120 ሺህ በላይ ዩኒት ደም መሰብሰቡን ገልፀዋል። በሌላ በኩል በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 153 የዓይን ብሌን መሰብሰቡን ጠቅሰው ከ1 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች የዓይን ብሌናቸውን ለመለገስ ቃል መግባታቸውንም አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል። የከፍተኛ 23 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር ሳሙኤል አሊ በበኩላቸው ደም በመለገስ ህይወት በማዳን ስራ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። አምና 350 ዩኒት ደም የትምህርት ቤቱ መምህራንና ተማሪዎች መለገሳቸውን ጠቅሰው ዘንድሮ እስከ 600 ዩኒት ደም ለመሰብሰብ እየሰራን ነው ብለዋል። በካቶሊክ ቅዱስ ዮሐንስ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ዲን የሆኑት መምህር ሃይለሚካኤል አፅበሃ በበኩላቸው በትምህርት ቤቱ የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ደም መለገስን ባህል በማድረግ በየዓመቱ እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የደም መሰብሰብ ስራን ለመጀመር ከደም ባንክ አገልግሎት ሰብሳቢ ባለሙያዎችን እየጠበቅን ነው ብለዋል። የአዲስ ከተማ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር እንዳልካቸው ደጀኔ በትምህርት ቤቱ ደም በመለገስ ህይወት የማዳን ስራ ባህል መሆኑን ተናግረዋል። ከአገልግሎቱ የሚሰጠውን ዕቅድ ለማሳካትና የትምህርት ቤቱ ተማሪዎችና መምህራን ደም እንዲሰጡ ለማስቻል ግንዛቤ በመፍጠር እየተዘጋጀን ነው ብለዋል።
የመረጃ ፍሰቱን በማጠናከር የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ እየተሰራ ነው
Oct 19, 2025 60
ወላይታ ሶዶ ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦የመረጃ ፍሰቱን በማጠናከር የምክክር ሂደቱን ውጤታማ የማድረግ ተግባር በተቀናጀ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ብሌን ገብረመድህን ተናገሩ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በወላይታ ሶዶ ከተማ "የሴቶች፣ የወጣቶች፣ እና የአካል ጉዳተኞች ሚና እና አስተዋጽኦ ለውጤታማ ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ብሌን ገብረመድህን እንደገለጹት ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው የመረጃ ፍሰቱን በማጠናከር የምክክር ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። ይህም መድረክ እስከ ታች ካሉ መዋቅሮች እና የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር የመረጃ ፍሰት ስርዓቱን ለማሳለጥና ግንዛቤን ለመፍጠር ያለመ ስለመሆኑ አመልክተዋል። ከዚህ ቀደም በአማራ፣ በድሬዳዋ፣ በሀረር፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ እና በሶማሌ ክልሎች ተመሳሳይ መድረኮች መካሄዳቸውን አስታውሰው ተደራሽነቱን በማስፋት የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም የመድረኩ ተሳታፊዎች የምክክር ሂደቱን ከዳር ሆነው ከመመልከት ይልቅ የወከሉትን ህዝብ ፍላጎት ተረድተው ባለቤትነቱ እስኪረጋገጥ መስራት እንደሚገባም መልዕክት አስተላልፈዋል። የደቡብ ኦሞ ዞን አካል ጉዳተኞች ተወካይ ህብስት መንክር በበኩላቸው ኮሚሽኑ በመሰል መድረኮች ሀሳባችንን እንድናቀርብ እና በአንድ ልብ እንድንሳተፍ እያከናወነ ያለው ተግባር የሚደነቅ ነው ብለዋል። ግጭትና አለመመግባባቶች በሚከሰቱበት ወቅት አካል ጉዳተኞች ግንባር ቀደም ተጠቂዎች እንደሚሆኑ ጠቁመው በሀገራዊ ምክክሩ የጎላ ተሳትፎ በማድረግ የአካል ጉዳተኞችን መብት ለማረጋገጥ እንሰራለን ሲሉ ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክር እንደ ኢትዮጵያ ላሉ በጦርነትና አለመግባባት አባዜ ውስጥ ለቆዩ ሀገራት ብርሃን ፈንጣቂ ነው ያለው ደግሞ የጎፋ ዞን ወጣቶች ተወካይ በኃይሉ በልጅጌ ነው። በመሆኑም ህዝቡ በተወካዮቹ በኩል የሰጠውን አጀንዳ የመፈጸም ኃላፊነት በኮሚሽኑ ላይ መጣሉን አክሎ ዕድሉን በመጠቀም ለኮሚሽኑ ስራ ስኬታማነት የበኩላችንን እንወጣለን ብሏል። በመድረኩም የሴቶች፣ የወጣቶች እና የአካል ጉዳተኞች ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ አካላት ተሳትፈዋል።
በጌዴኦ ዞን የነዋሪዎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ፍላጎት በዘላቂነት ለመመለስ እየተሰራ ነው
Oct 19, 2025 59
ዲላ ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን የማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ፍላጎት በዘላቂነት ለመመለስ የሚያስችሉ ተግባራት በቅንጅት እየተከናወኑ መሆናቸውን የዞኑ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ገለፀ። የመምሪያው ኃላፊ ዳዊት ጀቦ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት በዞኑ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማሳደግ በተደረገ ጥረት ውጤት ተገኝቷል። የዲላ ከተማን ጨምሮ በአራት ከተሞች የጥልቅ ጉድጓድ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማትን አጠናቅቆ ለአገልግሎት ማብቃትን ጨምሮ የተበላሹ 483 የውሃ ተቋማትን ጠግኖ ወደ አገልግሎት መመለስ መቻሉን አንስተዋል። በዚህም ከ96 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ተጠቃሚ በማድረግ የዞኑን የውሃ ሽፋን ከ10 በመቶ ወደ 40 በመቶ በላይ ማሳደግ እንደተቻለ ተናግረዋል። በተለይ በዞኑ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ገቢ የማመንጨት አቅማቸውን በማሳደግ ዘላቂ አቅርቦትን ከማረጋገጥ ባለፈ ተደራሽነታቸውን ለማስፋት በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። እንዲሁም ህብረተሰቡን እና አጋር አካላትን በማስተባበር በዞኑ ሁሉም መዋቅሮች የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውሃን በመጠቀም የንጹህ መጠጥ ውሃን ተደራሽ የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል። በዚህም በተያዘው ዓመት ከ100 ሺህ የሚልቁ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል። በዞኑ የይርጋጨፌ ወረዳ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰብስቤ ታምሩ በበኩላቸው በወረዳው ባለፈው አንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ 12 አዲስ የምንጭ ማጓልበትን ጨምሮ 470 የውሃ ተቋማት በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ መደረጉ የንጹህ ውሃ ተደራሽነትን አስፍቷል። በተያዘው ዓመት ማህበረሰብ አቀፍ የውሃ አስተዳደርን በማጠናከር ዘላቂ አቅርቦትንና ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተሠራ ነው ብለዋል። በወረዳው የንጹህ መጠጥ ውሃ ክፍያ ተመንን በማሻሻል ዘላቂ አቅርቦትን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የዲላ ዙሪያ ወረዳ የውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሜሪኩሪ ወልደየስ ናቸው። በተለይ የህብረተሰብ ተሳትፎን በማሳደግ በብልሽት ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ የውሃ ተቋማት ጥገና በማድረግ ወደ ስራ መግባታቸውን ተከትሎ የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋንን ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል። የዲላ ዙሪያ ወረዳ የሚችሌ ሆላና ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ አማረች ገዛኸኝ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም በንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር ምክንያት ለተለያዩ ውሃ ወለድ በሽታዎች ይጋለጡ እንደነበር አንስተዋል። ይህም በህብረተሰቡ ዘንድ የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ መቆየቱን አንስተው አሁን ላይ መንግስት የህብረተሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ጥያቄን በመረዳት ምላሽ እየሰጠ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ መጀመር ከእንግልት ታድጎናል - ተገልጋዮች
Oct 19, 2025 150
አሶሳ፤ ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ መጀመር ከብልሹ አሰራር እና እንግልት እንደታደጋቸው ተገልጋዮች ተናገሩ። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጳጉሜን 5/2017 ዓ.ም ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል። ማዕከሉ ሶስት የፌዴራል እና አምስት የክልል ተቋማትን አካቶ የተቀላጠፈ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በማዕከሉ ያገኘናቸው ተገልጋዮች መሶብ የምንፈልገውን አገልግሎት በአንድ ላይ እንድናገኝ ከማድረጉ በተጨማሪ ከብልሹ አሰራር ታድጎናል ብለዋል። የንግድ ስያሜ ለማውጣት ወደ ማዕከሉ የመጣው ወጣት አባቢያ ተስፋዬ እንደተናገረው፤ በማዕከሉ ያገኘው አገልግሎት ከዚህ ቀደም ሶስት የተለያዩ ተቋማት በመሄድ ይስተናገድ የነበረበትን ሁኔታ ያስቀረ ነው። የአንድ ማዕከል አገልግሎት በፌዴራል ደረጃ እንደተጀመረ በአጭር ጊዜ ወደ ክልሉ በመድረስ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ትልቅ ስኬት እንደሆነም ተናግሯል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመልካም አስተዳደር ችግር እንዲቀረፍ አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑን የተናገረው ወጣት አባቢያ በቀጣይ የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት የበለጠ ተደራሽ መሆን አለበት ነው ያለው። ከባምባሲ ከተማ የሙያ ፍቃድ ለማሳደስ የመጡት ወይዘሮ አለሚቱ ፉፋ በበኩላቸው፤ ወደ ማዕከሉ ሲመጡ ከአቀባበል ጀምሮ ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም የተለያዩ ምክንያቶችን በመስጠት ባለጉዳይን የማጉላላት ተግባር በብዛት ይስተዋል እንደነበር ጠቁመው አሁን ግን በመሶብ ማዕከል ሁሉንም አገልግሎት አግኝቻለው ብለዋል። ማዕከሉ የዲጂታል አገልግሎት በመስጠቱ ግልጽ እና ፍትሀዊ አገልግሎት ለማግኘት አስችሎናል ያሉት ደግሞ በማዕከሉ አዲስ ንግድ ፈቃድ ለማውጣት የተገኙት አብዱልከሪም ሰላማ ናቸው። መሶብ ከዚህ ቀደም በየተቋማቱ ይታይ የነበረውን የባለጉዳይ እንግልት በማስቀረት ፈጣን አገልግሎት በማግኘት እንድንስተናገድ የሚያደርግ ነው ብለዋል። የቤጉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሰመረ ጅራታ ማዕከሉ ስራ ከጀመረ ወዲህ በርካታ ተገልጋዮችን እያስተናገደ መሆኑን ተናግረዋል። ማዕከሉ አስፈላጊውን አገልግሎት እንዲሰጥ በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ እንዲሟላ መደረጉን ጠቅሰው፤ ባለሙያዎች ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ በቴክኖሎጂ የታገዘ ክትትል እና ቁጥጥር እንደሚደረግም አስረድተዋል።
ኢኮኖሚ
በሲዳማ ክልል ጤናማ የንግድ ሥርዓትን በመፍጠር የዋጋ ንረትን የመከላከሉ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 19, 2025 41
ሀዋሳ ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ጤናማ የንግድ ሥርዓት በመፍጠር የኑሮ ውድነት ጫናን የሚያቃልሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመላከተ፡፡ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የሕገ ወጥ ንግድ፣ ኮንትሮባንድና፣ የገበያ ንረት መከላከል የጋራ ግብረ ኃይል የንቅናቄ መድረክ አካሄዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የትምህርት ቢሮ ኃላፊና የግብረ ኃይሉ ሰብሳቢ አቶ በየነ በራሳ በክልሉ ጤናማ የንግድ ሥርዓትን በመፍጠር የኑሮ ውድነት ጫናን የማቃለል ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል፡፡ በክልሉ የምርቶች ነፃ ዝውውር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደሩ የሚገኙ ያልተፈቀዱ ኬላዎች የሚነሱ መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡ ለዚሁ ተግባር የተቋቋመው ግብረ ኃይልም በዚህ ረገድ ተቀናጅቶ በመስራት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት መወጣት እንዳለበትም ጠቁመዋል፡፡ የክልልና የፌዴራል ተቋማትን በቅንጅት ያቀፈው ግብረ ኃይሉ ባለፈው ዓመት ሕገወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎችንና የኮንትሮባንድ ንግድን የመከላከል ስራ ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሠላማዊት መኩሪያ ናቸው ፡፡ ቢሮው ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከጉምሩክ ኮሚሽን ሀዋሳ ቅርንጫፍ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ባደረገው የመከላከል ሥራ ከ145 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት የያዘ ሲሆን ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ እጃቸው ያለባቸውን አካላት በህግ ተጠያቂ የማድረግ ስራ መስራቱን አስረድተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በተለይ የነዳጅ ግብይቱን ሕጋዊነት ለመጠበቅ ብሎም በዕጥረት ምክንያት በህብረተሰቡ ላይ የሚከሰቱ ጫናዎችን ለማቃለል በየደረጃው በተቀናጀ መንገድ ስንሰራ ቆይተናል ብለዋል፡፡ ከነዳጅ ሕገወጥ ዝውውርና ንግድ ጋር በተያያዘ በ11 ማደያዎችና በ14 ሕገወጥ ነዳጅ ቸርቻሪዎች ላይ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ጠቁመው ከ70 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ በሕገወጥ መልኩ ሲዘዋወር መያዙን ገልፀዋል፡፡ በቡና፣ በሸቀጦችና በሌሎች ምርቶች ላይም እንዲሁ ጠንካራ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን የገለፁት ኃላፊዋ ያለፈው ዓመት ጉድለቶቻችንን በመገምገም በተያዘው በጀት ዓመት ይበልጥ የተጠናከረ የጋራ ሥራ እንሰራለን ብለዋል ፡፡ ባለፈው ዓመት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅተን በመስራታችን ውጤት ማምጣት ብንችልም ከችግሩ ስፋት አኳያ ብዙ ልንሰራቸው የሚገቡ ሥራዎች አሉ ያሉት ደግሞ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተስፋዬ ዴቢሶ ናቸው፡፡ ህብረተሰቡ ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን ለመከላከልና ለሕግ መከበር እየሰጠ ያለው ቀና ምላሽ የሚበረታታ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ ወንጀሎችን ህዝቡን በማሳተፍ በትኩረት ልንከላከላቸው ይገባል ብለዋል፡፡ በንቅናቄ መድረኩ ላይ የክልልና የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የፀጥታ አካላት እንዲሁም የዞን፣ የከተማ አስተዳደርና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በክልሉ በተቋማት መልሶ ግንባታ ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት መስጠት ተችሏል
Oct 19, 2025 33
ኮምቦልቻ ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በተለያዩ ዘርፎች መልሰው እንዲቋቋሙ በተደረጉ ተቋማት ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት መስጠት መቻሉን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር የሚያከናውነውን የመልሶ ማቋቋም ተግባር በኮምቦልቻ ከተማ ገምግሟል። የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን እንደገለጹት፣ በክልሉ በተለያየ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ተቋማትን በተሻለ ሁኔታ መልሶ የማቋቋም ስራ እየተከናወነ ነው። በክልሉ በጀት፣ በተለያዩ የልማት ድርጅቶችና አጋር አካላት ትብብር የመልሶ ማቋቋም ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም በርካታ የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃ፣ የግብርና፣ አስተዳደርና ሌሎችም ማህበራዊ ተቋማት በተሻለ ደረጃ መልሰው ተገንብተውና ተቋቁመው የተሻለ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል። የመልሶ ማደራጀት ስራው በሰላም እሴት ግንባታ እንዲሁም በሥራ እድል ፈጠራና ሌሎች ዘርፎችንም ውጤታማ ለማድረግ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። ሕብረተሰቡ አንድነቱንና ሰላሙን በማስቀጠል ተቋማትን መጠበቅና ለሕዝብ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ እንዳለበት አመልክተዋል። የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱ ሙሄ በበኩላቸው፣ በተለያየ ምክንያት የተጎዱ የውሃ፣ የትምህርት፣ የጤናና ሌሎችም ተቋማትን በተሻለ ሁኔታ መልሶ በማቋቋም ለሕብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እየተደረገ ነው ብለዋል። በዚህም በርካታ የመሰረተ ልማት ተቋማት በአዲስ መልክ ተገንብተው ጭምር ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል። በሰሜን ሽዋ ዞን የቀወት ወረዳ ገንዘብ ጽህፈት ቤት የፕሮጀክት ክትትልና ድጋፍ ባለሙያ አቶ አሸናፊ ጌታቸው በዞኑ በተለያየ ምክንያት የተጎዱ ተቋማት በተሻለ ደረጃ ተገንብተው ለሕብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የፃግብጂ ወረዳ ገንዘብ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ንጉስ ሙሉጌታ በበኩላቸው የተለያዩ ተቋማትን ደረጃ በማሻሻል ሕብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት ማግኘት ችሏል ብለዋል። በግምገማ መድረኩ የክልል፣ የዞንና ወረዳ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የአርባ ምንጭ የዓዞ እርባታን ለማዘመን የሚያስችል የ50 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክት ተቀርጾ ወደ ተግባር ተገብቷል
Oct 19, 2025 36
አርባምንጭ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የአርባ ምንጭ የዓዞ እርባታን ለማዘመን የሚያስችል የ50 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክት ተቀርጾ ወደ ተግባር መገባቱን የጋሞ ልማት ማህበር አስታወቀ። ማህበሩ በያዝነው በጀት ዓመት ከቱሪዝም እና ከቆዳ ሽያጭ እስከ 20 ሚሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት አቅዶ እየሠራ መሆኑም ተመላክቷል። የቱሪዝም አገልግሎት፣ የብዝሃ ሀብት ጥበቃ፣ የምርምርና የስራ ዕድል ፈጠራን ዓላማ በማድረግ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የአርባ ምንጭ የዓዞ ራንች የተመሰረተው በ1976 ዓ.ም ነው። ለ30 ዓመታት በመንግስት ሲተዳደር የቆየውን የዓዞ እርባታ (ራንች) የጋሞ ልማት ማህበር ተረክቦ ማስተዳደር ከጀመረ አንድ ዓመት የሆነው ሲሆን ማህበሩ ራንቹን ለማዘመን መጠነ ሰፊ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል። የጋሞ ልማት ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዋኖ ዋሎሌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ማህበሩ የዓዞ ቆዳ እና የቆዳ ውጤቶች ግብይት እንዲሁም የቱሪዝም ገቢ አቅምን ለማሳደግ የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎችን እያከናወነ ነው። የዓዞ እርባታው ሰፊ ቁጥር ያለው ዓዞ መያዝ እንዲችል ገንዳዎችን ማስፋፋትና ለቱሪስት ሳቢ እና ማራኪ ማድረግ ከስራዎቹ መካከል መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ቱሪስቶቹ በቆይታቸው የምግብና የመጠጥ አገልግሎቶችን የሚያገኙበት መናፈሻዎችን ለመገንባት እንዲሁም የዓዞ ቆዳ ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን አስረድተዋል። ከዚህ ቀደም ጎብኚዎች ዓዞዎችን ብቻ ሲጎበኙ እንደነበር ጠቁመው በአዲሱ ማሻሻያም ከዚህ በፊት ያልነበሩ እንደ ዘንዶ፣ ጥንቸል፣ ኤሊ እና ሌሎች እንስሳትን በማምጣት የቱሪዝም ዘርፉን ገቢን ለማሳደግ በስፋት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በጋሞ ልማት ማህበር የአርባ ምንጭ ዓዞ ራንች ኃላፊ ተወካይና አስጎብኚ አቶ አስደሳች ዳንኤል በበኩላቸው የዓዞ እርባታውን ዘመናዊ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ በመሆናቸው ሰፊ ለውጦች እየታዩ ነው ብለዋል። በዓዞ እርባታው በአሁኑ ወቅት ከ4 ሺህ በላይ ዓዞዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ከእነዚህ መካከል ከ2 ሺህ 700 የሚልቁት ለቆዳ ሽያጭ የደረሱ መሆናቸውን አስረድተዋል። በአርባ ምንጭ የዓዞ እርባታ ጉብኝት ሲያደርጉ ያገኘናቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪው አቶ ሽመልስ አረጋ ዓዞን ከዚህ ቀደም በፎቶ እና በቪዲዮ ብቻ ማየታቸውን ጠቅሰው ዓዞን በአካል ለማየት በመቻላቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። በዓዞ እርባታው የተጀመሩ የማሻሻያ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ጠቅሰው ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ያሉ የቱሪስት ፀጋዎችን መመልከትና ማወቅ እንዳለባቸውም አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ወንዞችና ቀይ ባሕር የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልጽግና የሚበይኑ ናቸው
Oct 19, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 9/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ወንዞችና ቀይ ባሕር የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልጽግና የሚበይኑ መሆናቸውን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ሳዲቅ አደም ገለጹ። በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በኢፌዴሪ መከላከያ ዋር ኮሌጅና በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትብብር "የሁለቱ የውሃ ሥርዓቶችና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ነፃነት፥ የዓባይና የቀይ ባሕር ትስስር እና የአፋር ክልልን ስትራቴጂካዊ ሚና መዳሰስ" በሚል መሪ ሃሳብ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ምክክር ተካሂዷል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ሳዲቅ አደም፥ የዓባይ ወንዝና ቀይ ባሕር የኢትዮጵያን ዕድገትና ብልጽግና የሚበይኑ ወሳኝ ወንዞች ናቸው ብለዋል። በዚህም በዓባይ ወንዝ ላይ የሙሉ ጊዜ መረጃ የሚያስተጋቡ ኃይሎች ኢትዮጵያን በቀይ ባሕር ጉዳይ አትናገሪ የማለት ምክንያትና መብት እንደሌላቸው ገልጸዋል። እኛ ኢትዮጵያውያን በዓባይ ወንዝ ላይ የነበረንን ቁዘማ ህዳሴ ግድብን በመገንባት መስበር ችለናል ሲሉም ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያን የቀይ ባሕር ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ የተጀመረውን ጥረት ሁሉም ዜጋ የጋራ አጀንዳ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። በትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር የፖሊሲና ስትራቴጂ ተመራማሪ ተመስገን ዋለልኝ(ዶ/ር)፥ አስተማማኝ የባሕር በር ማጣታችን በሎጀስቲክስና በትራንስፖርት ዘርፍ ውድ ዋጋ እያስከፈለን ነው ብለዋል። ይህም በወጪና ገቢ የንግድ ሥርዓት ላይ ጫና በማሳደር ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዳንሆን ከማድረጉ ባለፈ የኢኮኖሚ ዕድገታችን በሚፈለገው መልኩ እንዳይጓዝ እንቅፋት ሆኗልም ነው ያሉት። ኢትዮጵያውያን የባሕር በር መዳረሻ አለመኖር የሚያደርሰውን ተፅዕኖ በመገንዘብ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ በትብብር መስራት አለብን ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ተባባሪ ተመራማሪ ብሌን ማሞ፥ የባሕር በር ባለቤትነት ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ካለው ፋይዳ ባሻገር ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚፈጥረውን ዕድል ማየት እንደሚገባ ተናግረዋል። ቀጣናዊ የሰላምና መረጋጋት የኃይል ሚዛንን ለማስጠበቅም የኢትዮጵያን የባሕር ኃይልና የመከላከያ ሠራዊት በአስተማማኝ መሠረት መገንባት እንደሚያስፈልግም አጽነኦት ሰጥተዋል። የዓለም አቀፍ የህግ ተመራማሪው ደጀኔ የማነ፥ የመንግስታቱ ድርጅት ኢትዮጵያና ኤርትራን በኮንፌዴሬሽን ሲያዋህድ በርካታ ሀገራት የኢትዮጵያን ታሪካዊና ተፈጥሯዊ የባሕር በር እና የወደብ ባለቤትነት እንዲካተት አድርገዋል ብለዋል። የ2010 የኢትዮ-ኤርትራ ድንበር ኮሚሽን ውሳኔዎችና አጠቃላይ ሂደቶችን ታሳቢ በማድረግም በዓለም አቀፍ ሕግ ክርክር የማድረግ ዕድል እንዳላት አስረድተዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ስታርት አፕ ለስራ እድል ፈጠራ እድገት የሚኖረውን አቅም ለመጠቀም ምቹ መደላድል እየተፈጠረ ነው
Oct 19, 2025 83
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፡-ስታርት አፕ ለስራ እድል ፈጠራ እድገት የሚኖረውን አቅም ለመጠቀም ምቹ መደላድል እየተፈጠረ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለፁ። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የስታርት አፕ ስነ ምኅዳሩን ማስፋት የሚያስችል የክህሎት ልማት እና አዳዲስ የስራ ዕድል ፈጠራን የሚያበረታቱ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ አዳዲስ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች የሚወዳደሩበት "ብሩህ ኢትዮጵያ" የክህሎት ውድድር ሀገራዊ ልማትን የሚያሳልጥና ስታርት አፖችን ማፍራት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ባለፉት አራት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ 1 ሺህ 350 የፈጠራ ሀሳብ ላላቸው ዜጎች እውቅና ተሰጥቷል ብለዋል፡፡ በሀገሪቱ የሚኖረውን ፋይዳ አሟጦ ለመጠቀም አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብ ላላቸው ስታርት አፖች የመስሪያ ቦታ፣ የፋይናንስ፣ የአቅም ግንባታና ሌሎች ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡ የዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ስታርት አፕ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ ስታርት አፖች ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የስታርት አፕ ዘርፍ ኃላፊ ሙልጌታ ውቤ በበኩላቸው፤የወጣቶች የስራ ፈጠራ ዝንባሌ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ መንግስት የወጣቶችን ተሳተፎ ለማሳደግና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የስታርት አፕ አዋጅ በማጽደቅ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል፡፡ የፈጠራ ሀሳቦች ስታርት አፕ መሆናቸው በህግ ተለይቶ ምዝገባና ስያሜ ከተሰጠ በኋላ አስፈላጊው የፋይናንስና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ አዋጁን ገቢራዊ ለማድረግ ሀገር አቀፍ የስታርት አፕ ፖርታል እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸው፤ የማስፈጸሚያ ደንቦችና መመሪያዎች ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሸገር ከተማ ለተገልጋዮች ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Oct 18, 2025 87
ሸገር፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተገልጋዮች ተናገሩ። በሸገር ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ከተመዘገቡት ከ11ሺህ 224 ተገልጋዮች አብዛኞቹ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን እንደገለጹም ተመላክቷል። ከተጠቃሚዎቹ መካከል በአስተዳደሩ የፉሪ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሁዳ አብዱልከሪም፤ በአሁኑ ወቅት በማዕከሉ እያገኙት ያለው አገልግሎት በእጅጉ መሻሻሉን ለኢዜአ ተናግረዋል። ከዚህ በፊት አገልግሎት ለማግኘት ውጣ ውረድ ብሎም ላልተገባ ወጪ ሲዳረጉ እንደነበር አውስተው፤ አሁን ላይ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚፈልጉትን አገልግሎት በማግኘት ምቹ ሁኔታ አንደተፈጠረላቸው ገልጸዋል። ቀደም ሲል በነበረው አገልግሎት ፋይል የመጥፋት አጋጣሚና ሌሎችም ችግሮች እንደነበር በማስታወስ አስተያየት የሰጡት ደግሞ ከገላን ክፍለ ከተማ የመጡ አቶ ወርቅነህ በንቲ ናቸው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ አገልግሎት ሰጪ ባለሙያዎቹ መልካም ስነምግባር በመላበስ ከአስር ደቂቃ በታች ግልጽና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት እንደሚያስተናግዱና በዚህም መደሰታቸውን ተናግረዋል። ሌላው ተገልጋይ ከኩራጅዳ ክፍለ ከተማ የመጡት አቶ ሀብታሙ ጆቴ፤ በከተማው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ከ15 ደቂቃ ባነሰ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እያገኙ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ አስተዳደር የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኦፕሬሽን ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ካሳሁን ጆብር እንዳሉት፤ ቀደም ሲል በከተማው የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በተበታተነና በተራራቀ መልኩ የሚያካሄዱት አሰራር በቴክኖሎጂ ያልተደገፈና የመረጃ ስርዓቱ ያልተሟላ ነበረ ። አገልግሎቱን ለማሻሻል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በማስጀመር የሚያስፈልጉትን ቴክኖሎጂና የሰው ሃይል በማሟላት ለማሕበረሰቡ ተደራሽ፤ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል። ይህ አሰራር ከተጀመረ በሶስት ወራት ውስጥም ከተመዘገቡት ከ11ሺ224 ሰዎች ውስጥ አስር ሺህ ሰዎች አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣይ አገልግሎቱን የበለጠ በማስፋፋት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፤ ለባለሙያው የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ተገልጋዮች የሚጠበቅባቸውን አሟልተው እንዲገኙ ግንዛቤ ከመስጠት ጎን ለጎን በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መመቻቸቱን አስረድተዋል። በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ከሸገር ከተማ በተጨማሪ በቢሾፍቱ፤ አዳማ፤ ሻሸመኔና ጅማ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩ የሚታወስ ነው።
የልህቀት ማዕከሉ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የሚቆም ሚዲያ እና ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተላበሰ ጋዜጠኛ ለመፍጠር ያስችላል
Oct 18, 2025 107
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡- የሚዲያ ልህቀት ማዕከል ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የሚቆም ሚዲያ እና ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተላበሰ ጋዜጠኛ ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ለሀገር ግንባታ፣ ለዜጎች የመረጃ ተደራሽነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና እንዲኖረው የዓለምን ነባረዊ ሁኔታ የዋጀ የዘርፉ ባለሙያ እና ቴክኖሎጂ መታጠቅ አለባቸው፡፡ በኢትዮጵያ ከለውጡ በኋላ የመገናኛ ብዙኃንና ጋዜጠኞች ዘርፉ የሚጠይቀውን ሙያዊ ሥነ ምግባር ተላብሰው ለሀገር ግንባታና ለዜጎች ተደራሽነት በነፃነት መስራት የሚችሉባቸው የህግና የአሰራር ማሻሻያዎች ተደርገዋል፡፡ በቅርቡም የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን ዕውቀትና ክህሎት በምርምር፣ በማማከርና ስልጠና ማሳደግ የሚያስችል የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ሥራ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ አዲስ አበባን ጨምሮ በ25 ዩኒቨርሲቲዎች የጋዜጠኝነት ትምህርት እየተሰጠ ነው፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርቱን መስጠታቸው ትልቅ ነገር መሆኑን ያወሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ሆኖም አብዛኞቹ የጋዜጠኝነት ምሩቃን የንድፈ ሃሳብ እንጂ የተግባር ዕውቀትና ክህሎት እንደሚጎድላቸው ለይተናል ብለዋል፡፡ ጋዜጠኝነት ጽንሰ ሀሳቡን ተረድቶ ትንታኔ መስጠትና ማብራራት ቢሆንም ክፍተት ይታያል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በሥራ ላይ ያሉ ጋዜጠኞች ተለዋዋጭ ከሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር በየጊዜው መዘመን እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ውስን ዓላማን ብቻ ለማስፈፀም እንደነበር ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ምን ዓይነት ጋዜጠኝነት ትፈልጋለች የሚለውን መመለስ የሚያስችል የተቀናጀ ስልጠና አልነበረም ብለዋል፡፡ ጋዜጠኝነት ከዓለም ነባራዊ አውድ ጋር የተጣጣመ ቀጣይነት ያለው ዝማኔ ይፈልጋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የኢትዮጵያ የሚዲያ ልህቀት ማዕከልን ማቋቋም ማስፈለጉን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ኢትዮጵያን የሚመስል ዘመኑን የዋጀ የመገናኛ ብዙኃንና የጋዜጠኝነት ሙያ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ግቡ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ለሀገር ግንባታ የሚቆም፣ ለዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚተጋ የመገናኛ ብዙኃንና ጋዜጠኛ ማፍራት መሆኑን አንሰተዋል፡፡ በዚህም የልህቀት ማዕከሉ በብቁ የሰው ሀይል እና በቴክኖሎጂ የተሟላ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ጋዜጠኛውን ብቻ ሳይሆን መገናኛ ብዙኃንን ጭምር እንዲያልቅ እንፈልጋለን ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በጥናትና ምርምር፣ ስልጠናና በማማከር ሀገር በቀል እሳቤዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በዓለም ላይ ጋዜጠኝነት ከጥቅል ወደ ልዩ ዘጋቢነት እየተቀየረ መሆኑን በማስታወስ፤ ጋዜጠኞችን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በምርጫ፣ ውሃ፣ ፋይናንስ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ አቬሽን ጋዜጠኝነትና መሰል ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በማሰልጠንና በማብቃት የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ማዕከሉ የምርጫ ጋዜጠኝነት ስልጠና በቅርቡ እንዲሚጀምር በመጥቀስ፤ ከስድስት ዩኒቨርሲቲዎች በመጡ 32 ፕሮፌሰሮች 11 የሥልጠና ሰነዶች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ለሶስት ወራት በሚሰጠው የምርጫ ጋዜጠኝነት ሥልጠና የተዘጋጁ ሰነዶች የኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ፣ ሚዲያና ዲሞክራሲ፣ ሚዲያና ብሔራዊ ጥቅም፣ ምርጫና የዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ልምድ፣ እንዲሁም ሚዲያ ማህበረሰብና ባህል የሚሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትን ለማጠናከር በሚደረገው ሂደት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ ይገባል
Oct 18, 2025 91
ጅማ ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡-የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትን ለማጠናከር በሚደረገው ሂደት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አስታወቀ። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር "የሳይበር ደህንነት የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት" በሚል መሪቃል በጅማ ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል። የሳይበር ደህንነት ወርን በማስመልከት በተዘጋጀው በዚህ የውይይት መድረክ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን መድረኩም ግንዛቤ የመፍጠር ዓላማ እንዳለው ተመላክቷል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ዲጂታል የመንግስት አገልግሎትን ለማስፋፋት ትኩረት ከመስጠት ባለፈ በሳይበር ደህንነት ላይ ጠንካራ ሥራ እየተሰራ ነው። ተቋማቱም የሳይበር ደህንነት ተጋላጭነታቸውን በመቀነስ አስተማማኝ እና ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ትኩረት መሰጠቱን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል። የዲጂታላይዜሽን አገልግሎት ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የሁልግዜም ተግባር ሊሆን እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። የሳይበር ደህንነትን ወርም ይህን እውን ለማድረግና የሀሰተኛ የመረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር በማለም እንደሚከበር አክለዋል። በተለይም የስማርት ከተማን በመገንባት ፈጣንና ዘመናዊ አገልግሎቶችን ለመስጠትና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ የዲጂታል አገልግሎት ጉልህ አስተዋጾ እንዳለው ነው የገለጹት። ለተግባራዊነቱም ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትን ለማጠናከርና የስማርት ከተሞችን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በብልጽግና ፓርቲ የጅማ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ዋሴ ግርማ በበኩላቸው እንዳሉት በጅማ ከተማ ዲጂታል አገልግሎቶችን በመተግበር ስማርት ከተማ ለመገንባት እየተሰራ ነው። ለእዚህም ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር በከተማዋ ፈጣንና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ የተለያዩ ተቋማት የሥራ ሀላፊዎች እንዲሁም የፌደራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸው ታውቋል።
ስፖርት
የታሪካዊ ባላንጣዎቹ ፍልሚያ በአንፊልድ ሮድ
Oct 19, 2025 75
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የስምንተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ሊቨርፑል እና ማንችስተር ዩናይትድ ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከምሽቱ 12 ሰዓት ከ30 በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም ይካሄዳል። ሊቨርፑል በሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው ሰባት ጨዋታዎች 5 ጊዜ ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። ቡድኑ በጨዋታዎቹ 13 ግቦችን ሲያስቆጥር 9 ግቦችን አስተናግዷል። ቀያዮቹ በ15 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። ተጋጣሚው ማንችስተር ዩናይትድ በበኩሉ በሊጉ ባካሄዳቸው 7 ጨዋታዎች 3 ጊዜ ሲያሸንፍ በተመሳሳይ 3 ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪው አንድ ጨዋታ ነጥብ ተጋርቷል። ቡድኑ በጨዋታዎቹ 9 ግቦችን ሲያስቆጥር 11 ጎሎች ተቆጥረውበት በ10 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሁለቱ ክለቦች እስከ አሁን በሁሉም ውድድሮች 219 ጊዜ ተገናኝተው ማንችስተር ዩናይትድ 85 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ሊቨርፑል 73 ጊዜ በማሸነፍ 61 ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። ሁለቱ ክለቦች በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ባደረጓቸው 62 ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ 28 ጊዜ ሲያሸንፍ ሊቨርፑል 19 ጊዜ አሸንፎ 15 ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። በአንጻሩ ማንችስተር ዩናይትድ በውጤት ማጣት ቀውስ ውስጥ ሲሆን በፕሪሚየር ሊጉ ባለፉት ሶስት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል። ለ131 ዓመታት የዘለቀ ታሪካዊ ተቀናቃኝነት ያላቸው ሁለቱ ክለቦች በተመሳሳይ የሊጉን ዋንጫ 20 ጊዜ በማንሳት ስኬታማ ክለቦች ናቸው። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ሊቨርፑል የዛሬው ጨዋታ ከሁለት ተከታታይ የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርገው ፍልሚያ ነው። ቡድኑ ካሸነፈ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አንድ ዝቅ ያደርጋል። ተጋጣሚው ማንችስተር ዩናይትድ ካሸነፈ በሩበን አሞሪም ስር በሊጉ ለመጀመሪያ ጊዜ ተከታታይ ድል ያስመዘግባል። የ40 ዓመቱ እንግሊዛዊ ማይክል ኦሊቫር ወሳኙን ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌላኛው የሊጉ መርሃ ግብር ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከአስቶንቪላ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
የኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ 51ኛው የፕሪሚየር ሊግ የደርቢ ጨዋታ ዛሬ ይጠበቃል
Oct 19, 2025 79
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚያደርጉት የደርቢ ጨዋታ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን ቀልብ ስቧል። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከቀኑ 9 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል። ቡድኖቹ በሊጉ እርስ በእርስ ሲገናኙ የአሁኑ ለ51ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም 50 ጊዜ ተጫውተው ቅዱስ ጊዮርጊስ 21 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ኢትዮጵያ ቡና 9 ጊዜ ድል ቀንቶታል። 20 ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። በ50ዎቹ ጨዋታዎች በድምሩ 97 ጎሎች የተቆጠሩ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ 63 እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና ደግሞ 34 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ሁለቱ ክለቦች በ2017 ዓ.ም የውድድር ዓመት ባደረጓቸው ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ቡና አንድ ጊዜ ሲያሸንፍ በቀሪው ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል። በ2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ቡና በ60 ነጥብ ሁለተኛ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ49 ነጥብ 9ኛ ደረጃን ይዘው ማጠናቀቃቸው የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ ቡና የሊጉን ዋንጫ አንድ ጊዜ ያነሳ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ 16 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። የሁለቱ ክለቦች በርካታ ደጋፊዎች ለጨዋታው ድምቀት ይሰጡታል ተብሎ ይጠበቃል። በሌሎች መርሃ ግብሮች ፋሲል ከነማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቀኑ 9 ሰዓት፣ መቻል ከወላይታ ድቻ ከምሽቱ 12 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በደርቢው ጨዋታ ባየር ሙኒክ ቦሩሲያ ዶርትሙንድን አሸነፈ
Oct 18, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦ በጀርመን ቡንድስሊጋ የሰባተኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሃ ግብር ባየር ሙኒክ ቦሩሲያ ዶርትሙንድን 2 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በአሊያንዝ አሬና ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሃሪ ኬን እና ማይክል ኦሊሴ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጁሊያን ብራንድ ለዶርትሙንድ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ ባየር ሙኒክ በ21 ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። በሊጉ የመጀመሪያ ሽንፈቱን ያስተናገደው ቦሩሲያ ዶርትሙንድ በ14 ነጥብ ከነበረበት ሁለተኛ ደረጃ ወደ አራተኛ ዝቅ ብሏል።
አርሰናል የሊጉን መሪነት ዳግም ተረከበ
Oct 18, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የስምንተኛ ሳምንት መርሃ ግብር አርሰናል ፉልሃምን 1 ለ 0 ተሸንፏል። ማምሻውን በክራቫን ኮቴጅ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሊያንድሮ ትሮሳርድ በ58ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ አሳርፏል። አርሰናል በሊጉ ከማዕዘን ምት ያስቆጠራቸው የግቦች ብዛት ሰባት አድርሷል። በሊጉ ስድስተኛ ድሉን ያስመዘገበው አርሰናል በ19 ነጥብ የሊጉን መሪነት ከማንችስተር ሲቲ ተረክቧል። በውድድር ዓመቱ አራተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ፉልሃም በስምንት ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል።
አካባቢ ጥበቃ
በአማራ ክልል ከ260 ሺህ ሄክታር በሚልቅ መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውሃ እቀባ ሥራ ይከናወናል
Oct 18, 2025 102
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዚህ ዓመት ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውሃ እቀባ ስራዎች እንደሚከናወኑ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ገለጹ። የአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ንቅናቄ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በደብረ ብርሃን ከተማ ልቼ ቀበሌ ተካሂዷል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) የተፈጥሮ ሀብት ልማት እና ጥበቃ ስራ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ካልመጣ የመስኖ ስራ ውጤታማ እንደማይሆን ገልጸዋል። ክልሉ በመስኖ መልማት የሚችል ሰፊ አቅም እንዳለው ተናግረዋል። ይህንን ታሳቢ በማድረግ በዚህ ዓመት ከ52 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዲስ መስኖ በማስገባት የክልሉን የመስኖ ልማት ወደ 383 ሺህ ሄክታር ከፍ ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቁመዋል። ከተፈጥሮ ሀብት ልማት እና ጥበቃ ስራዎች አንጻርም በዚህ ዓመት ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ እቀባ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። ይህንንም ለማድረግ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን የሚሆን የደን እና የፍራፍሬ ችግኝ ልማት እቅድ ተይዞ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል። የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ዝግጅቶቹ የመስኖ አውታር ግንባታ፣ የቅየሳ፣ የአርሶ አደሮች ስልጠና እንዲሁም የችግኝ ጣቢያዎች ግንባታ እና የእርሻ መሳሪያ ዝግጅቶችን ያካተተ መሆኑን አንስተዋል። በተደረጉ ጥናቶች ክልሉ በመስኖ ሊለማ የሚችል 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት እንዳለው ገልጸዋል። ይህንን ለማልማትም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ ረገድ ባለፉት ዓመታት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። በርካታ የውሃ መሳቢያ መሳሪያዎች ወደ ዞኖች እና ወረዳዎች መከፋፈሉን ገልጸው ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል ስራ መሆኑን ገልጸዋል።
ምርታማነትን ለማሳደግ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብና የአፈርና ውሃ ጥበቃን ማጠናከር ይገባል
Oct 18, 2025 84
አዳማ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፡-ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብና የአፈርና ውሃ ጥበቃን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ። የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ የንቅናቄ ሳምንት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ዛሬ ተጀምሯል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ገመቹ በወቅቱ እንዳመለከቱት፥ በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራዎች የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር፣ድርቅና የጎርፍ አደጋዎችን ለመመከት አግዘዋል። በተለይም በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኖችን የመንከባከቡ ስራ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ለመቋቋምና የተራቆቱ መሬቶች እንዲያገግሙ፣የደረቁ ሃይቆች፣ወንዞችና ዥረቶች ተመልሰው ለመስኖና ለተለያዩ ልማቶች እንዲውሉ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። በበጋ ወቅት የተገነቡ የተፋሰስ ልማቶችን በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ በመሸፈንና በመንከባከብ ውጤት መገኘቱንም አንስተዋል። ተግባሩንም ለማዝለቅ የችግኝ እንክብካቤ የንቅናቄ ሳምንትን በማወጅ በዛሬው ዕለት የክልሉ ግብርና ሴክተር አመራሮችና ሰራተኞች በምስራቅ ሸዋ ዞን ማስጀመራቸውን ጠቁመዋል። በችግኝ እንክብካቤው አረም በማንሳት፣የመኮትኮትና ውሃን በማጠጣት ችግኞቹ የበጋውን ወቅት እንዲቋቋሙ መስራት ይገባል ብለዋል። በንቅናቄው ማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉት ከድር መሐመድ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ እንዲያድጉ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ችግኝ መትከል ብቻውን ግብ እንዳልሆነ ተናግረው፤የተተከሉትን ችግኞች በየጊዜው በመንከባከብ ለውጤት እንዲበቁ ማድረግ አለብን ብለዋል። ዘርፌ ማሞ በበኩሏ፥ በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ በቀዳሚነት የሚጎዱት ሴቶች በመሆናቸው ለመፍትሔው ላለፉት ሰባት ዓመታት በችግኝ ተከላና እንክብካቤ ላይ መሳተፋቸውን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ ናት- ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)
Oct 16, 2025 173
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርኃ ግብር አካሂዷል። በመርኃ ግብሩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያሥላሴ፣ ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተገኝተዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ምላሽ ለመስጠት ያለንን ቁርጠኝነት ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል። ጉባዔው አፍሪካውያን ለአየር ንብረት ለውጥ ተጨባጭ መፍትሔዎችን በመውሰድ ግንባር ቀደም መሆናቸውን ለዓለም በማሳየት ስኬታማ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም ለጋራ ችግሮች በጋራ ምላሽ ለመስጠት አቅማቸውን ያጠናከሩበት እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ይህን ስኬት ተጠቅሞ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት የሥራ ዕድል ፈጠራ ውጤታማ ተግባር እያከናወነች ትገኛለች
Oct 16, 2025 142
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ከአካባቢ ጥበቃ ባሻገር ከፍተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል በአፍሪካ ግንባር ቀደም የሆነ ተግባር እያከናወነች መሆኑ ተገለጸ። ይህ የተገለጸው "አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችና ወጣቶች" በሚል ርዕስ በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የተጠና ጥናት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ይፋ በሆነበት መድረክ ላይ ነው። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት እና የጥናቱ መሪ ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና እንደገለጹት የአረንጓዴ ልማት ስራ ዕድል ፈጠራ የአካባቢን ዘላቂነት ከማረጋገጥ ባሻገር ለወጣቶች ከፍተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል ወሳኝ ሚና አለው። ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የአካባቢ ጥበቃን በማጠናከር ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር በአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ተግባር እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይ በአረንጓዴ ልማት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል በሁሉም ሴክተሮች በማስፋት የወጣቱን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማትን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል። በመሆኑም በተለይ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የአረንጓዴ የስራ ዕድል የሚፈጥሩ ስልጠናዎች ተገቢ ትኩረት እንዲያገኙ እንዲሁም በፖሊሲዎች ውስጥ ልዩ ትኩረት እንዲሰጣቸው በማድረግ ሊበረታቱ እንደሚገባም አመልክተዋል። የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለበል ደሴ በበኩላቸው፣ ጥናቱ የኢትዮጵያን አረንጓዴ ዕድገት ስትራቴጂዎችና የወጣቶች የሥራ ስምሪት ዕቅዶችን እንደሚደግፍ ጠቅሰዋል። ግኝቶቹ ወደ ተግባራዊ ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞች እንዲተረጎሙ ከሚመለከታቸው የመንግስት መሥሪያ ቤቶች እና የልማት አጋሮች ጋር በቀጣይ እንደሚሰራበት ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ የአካባቢ ጥበቃን የሚያጠናክር አረንጓዴ ሥራዎች ሙያዊ ሥልጠና ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የአካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ገነነ አበበ(ዶ/ር) ናቸው። በቀጣይ የአረንጓዴ ሥራን ይበልጥ ለማስፋፋት በተለይ በቀጣሪ መሥሪያ ቤቶችና ሌሎች ተቋማት ላይ የግንዛቤ ሥራ ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በቁርጠኝነት ሊተገብሩ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት
Oct 19, 2025 88
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) አፈጻጸም ውጤታማነት ለማሳደግ በትኩረት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብስባ ከጥቅምት 11 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች እና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገም እና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስ እና ዘላቂ የውሃና ተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩ ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚከናውን ኢዜአ ከህብረቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ
Oct 15, 2025 275
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር እና በአህጉሪቷ የማካካሻ ፍትህን ለማረጋገጥ በበለጠ ቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን በአፍሪካ ደረጃ ዛሬ በአህጉሪቷ መዲና አዲስ አበባ ዛሬ ይከበራል። “የገጠር ሴቶችን በማካካሻ ፍትህ አማካኝነት ማብቃት፤ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ስርዓተ ምግብን ማረጋገጥ” የቀኑ መሪ ሀሳብ ነው። በቀኑ አከባበር ላይ የአፍሪካ ህብረት አመራሮች፣ የመንግስታት ተወካዮች፣ የገጠር ሴቶች አመራሮች እና ተወካዮች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ የዳያስፖራ ተወካዮች፣ የልማት አጋሮች እና የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ይሳተፋሉ። የቀኑ አከባበር አካል የሆነ የቴክኒክ ውይይት ትናንት የተካሄደ ሲሆን የአፍሪካ የገጠር ሴቶች መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ባለሙያዎች ሴቶችን ለማብቃት በየሀገራቱ እየተተገበሩ ያሉ ኢኒሼቲቮችን አስመልክቶ የእውቀት እና የተሞክሮ ልውውጥ አድርገዋል። ዛሬ በሚኖረው ዋናው የቀኑ አከባበር የከፍተኛ ባለስልጣናት ቁልፍ ንግግሮች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የገጠር ሴቶች ኢኒሼቲቭ የተሞክሮ ማጋራት መርሃ ግብሮች እና አውደ ርዕዮች ይካሄዳሉ። ሁነቶቹ የገጠር ሴቶች በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እና በግብርና መካናይዜሽን አማካኝነት የሚበቁባቸው የኢኖቬሽን አማራጮች የሚቀርቡባቸው ናቸው። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን ከአፍሪካ ህብረት የ2025 መሪ ሀሳብ ከሆነው “የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” የተሳሳረ መሆኑ ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የማሻሻሻ ፍትህ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል አካሄድ መሆኑን አመልክቷል። የቀኑን አከባበር ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የጋራ መግለጫው አፍሪካ ስርዓተ ጾታን ባማከለ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ስራ፣ የገጠር ሴቶችን በማብቃት እንዲሁም ማካካሻ ፍትህ እኩልነት የተረጋገጠበትና የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመገንባት ያላትን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያመላክት እንደሆነ ተገልጿል። የዓለም የገጠር ሴቶች ቀን የአፍሪካ ህብረት የስርዓተ ጾታ እኩልነት ለማረጋገጥ እና በማካካኛ ፍትህ አማካኝነት በገጠሪቷ የአፍሪካ አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። ህብረቱ ቀኑን ሲያከብር የበለጸገች፣ ሁሉን አቃፊ እና ዘላቂነትን ያረጋገጠች አህጉር ለመገንባት ባለው መሻት ውስጥ ሴቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ወደኋላ እንዳይቀሩ ዳግም ቃል ኪዳኑን የሚያድስበት እንደሆነ አመልክቷል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እ.አ.አ በ2007 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ባፀደቀው የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 62/136 አማካኝነት ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን እ.አ.አ ኦክቶበር 15 እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ በገጠር የሚገኙ ሴቶች ለግብርና፣ ምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ዘላቂ ልማት ያላቸው ወሳኝ አበርክቶዎች የሚዘከርበት ነው።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በሙሉ አቅም መተግበር ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው - መሐመድ አሊ ዩሱፍ
Oct 10, 2025 412
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ሙሉ ለሙሉ ገቢራዊ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 24ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሁነቶች በአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት እና ተወዳዳሪነት ተጽእኖ እያሳደሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከመቼው ጊዜ በላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሙሉ ለሙሉ በአፋጣኝ መተግበር እንደሚገባው የሚያመላክት ነው ብለዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ከቀረጥ ጋር ያልተያያዙ የንግድ ገደቦችን በማንሳት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተሳለጠ የንግድ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችሉ ማዕቀፎችን በመተግበር ለአጀንዳ 2063 መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኮሜሳ፣ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (ሳዴቅ) እና የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ (ኢኤሲ) የሶስትዮሽ ትብብር ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ማዕቀፉ የትስስር አጀንዳ ተምሳሌት እና አንድ የሆነች፣ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች አህጉር ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ የተስፋ ብርሃን ፈንጣቂ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር ቀጣናዊና አህጉራዊ የትስስር አጀንዳዎችን ትግበራ ለማፋጠን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንደሚያጠናክሩ ገለጹ
Oct 10, 2025 380
አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን የቆየ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። ጀርመን ለኢጋድ ቀጣና የተለያዩ የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፎችንም ይፋ አድርጋለች። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በልማት ትብብራቸው ዙሪያ በጅቡቲ ስትራቴጂካዊ ምክክር አድርገዋል። በምክክሩ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር እና ልማት ሚኒስቴር የምስራቅ አፍሪካ ዘርፍ ኃላፊ ሃኒንግ እና በጅቡቲ የጀርመን አምባሳደር ሄይከ ፉለር (ዶ/ር) ተገኝተዋል። ስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ የግንኙነት ማዕቀፎች ላይም መክረዋል። ፍልሰት እና አየር ንብረት ለውጥ የውይይቱ አበይት ማጠንጠኛዎች ናቸው። ሁለቱ ወገኖች የጀርመን ቀጣናዊ የፍልሰት ፈንድ ዳግም ማዋቀር ሂደት መልካም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በማንሳት የኢጋድ የቀጣናዊ የፍልሰት ፖሊሲ ማዕቀፍ ፣ የነጻ እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፎች እና የዜጎችን የአኗኗር ሁኔታ የማጠናከር ስራ ለመደገፍ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ጀርመን ለኢጋድ የፍልሰት ፖሊሲ ትግበራ ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ ትግበራ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ ቃል መግባቷን ኢዜአ ከቀጣናዊ ተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም ጀርመን በኢጋድ አባል ሀገራት ለሚከናወኑ የማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ስራዎች በቀጣናዊ የአደጋ ፋይናንስ ፕሮግራም አማካኝነት 22 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ መዘጋጀቷ ተመላክቷል። የፋይናንስ ማዕቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ድንገተኛ አደጋዎችን የመከላከል ስራዎች የሚደገፍ እና የኢጋድ የድርቅ አደጋን የመቋቋም እና ዘላቂነት ኢኒሼቲቭ ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን የሚደግፍ ነው። በስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች ውጤት ተኮር፣ አሳታፊ እና ተጠያቂነትን መሰረት ያደረገ አጋርነትን መፍጠር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢጋድ እና ጀርመን ትብብራቸውን ለማጠናከር፣ የጋራ ስራዎቻቸው የአባል ሀገራት የቅድሚያ ትኩረቶች ያማከሉ እንዲሆኑና የፖሊሲ ምክክራቸውን በመደበኛነት ለማከናወን ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ኢጋድ እና ጀርመን 37 ዓመታትን ያስቆጠረ አጋርነት እንዳላቸው መረጃዎች ያመለክታሉ።
ሐተታዎች
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 269
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል። ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው። የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው። ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል። ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 424
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም። በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል። የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል። በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል። በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል። በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 625
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
"ያሆዴ"- ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት
Sep 28, 2025 712
(በማሙሽ ጋረደው - ከኢዜአ ሆሳዕና ቅርንጫፍ) የሀዲያ የአዲስ ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው። ለማህበራዊ የህይወት አመራር ጉልህ አስተዋጾም ስላለውም በሀዲያዎች ዘንድ በየዓመቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል፡፡ "ያሆዴ" ያለፈውን አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲስ ዘመን የሚቀበሉበት፤ የመጻኢ ተስፋ ብስራትና የልምላሜ ምልክትም ጭምር ተደርጎም ይቆጠራል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሲቀርብ የሀዲያ ተወላጆችና የበዓሉ ተሳታፊዎች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከያሉበት ወደአካባቢው በመምጣት ይሰባሰባሉ፡፡ በዘንድሮ የያሆዴ በዓልም የሀድያ ተወላጆች የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ በተዘጋጀ ስፍራ (ነፈራ) ተሰባስበው በዓሉን በድምቀት አክብረውታል፡፡ በበዓሉ አከባበር ያለፈው ዓመት ስኬትም ይገመገማል፤ በአዲሱ ዓመትም የተሻለ ተሰርቶ ስኬት እንዲመዘገብ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት ይካሄዳል። ሊተገበር የሚችል ዕቅድም ይታቀዳል፡፡ በግልና በቤተሰብ የመጡ ስኬቶች በጋራ በመሆን ይገመገማሉ። የበረቱና ውጤት ያስመዘገቡም እንዲበረታቱ ይደረጋል። ለዚህም ነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው የሚባለው። ሰዎች እንዲሰሩና ስኬት እንዲያስመዘግቡ የሚያበረታታ እሴት አለው። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፋን ቦጋለ እንደሚሉት የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል "ያሆዴ" ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት ነው፡፡ ከነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የበዓሉ መቃረብን የሚያበስሩት ታዳጊ ልጆች ናቸው። ልጆቹ የዋሽንት (ገምባቡያ) ድምጽ ማሰማት ከጀመሩ በጉጉት የሚጠበቀውን የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል መድረሱ ምልክት ነው። በዓሉ ሀድያዎች አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበት ወቅት ነው። በዓሉ የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት በመሆኑም የተለየ ትርጉምና ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች ተራርቀው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት ከያሉበት ይሰባሰባሉ። በዓሉ በአማረ መልኩ እንዲከበርም ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻቸውን ያከናውናሉ። አባውራዎች ለበዓሉ ሠንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በቱታ ወይም በቅርጫ ቡድናቸው አማካኝነት እየቆጠቡ ይቆያሉ። እንዲሁም ለእንስሳት የሚሆን የግጦሽ ሳር የሚያበቅል ቦታ ከልለው ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሚሆነበት ምክንያት ደግሞ በዓሉ በሚከበርበት ሰሞን የሰው ልጅ ይቅርና እንስሳትም መጥገብ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ እማውራዎች ከበዓሉ ሦስትና አራት ወራት አስቀድመው እንሰት በመፋቅ ቆጮና ቡላ ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም ከአካባቢው እናቶች በጋራ በመሆን (ዊጆ) የተሰኘ የቅቤ እቁብ በመግባት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ማጠራቀም ይጀምራሉ፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ ለአተካናና ለሥጋ መብያ ናቀሮ ወይም ዳጣን እንዲሁም የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት ድርሻ የእናቶች ነው፡፡ ለበዓሉ የቤት ውስጥና የውጭ ግርግዳን በቀለምና በተለያዩ ጌጣጌጦች የማስዋብ ሃላፊነት ደግሞ የልጃገረዶች ነው። ወጣት ወንዶች ከነሀሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚያሳዩዋቸውን ግንድ በመቁረጥ ለምግብ ማብስያ እንዲውል ፈልጠው ያዘጋጃሉ። በሀዲያዎች አጠራር ለችቦ የሚሆን እንጨት ወይም ጦምቦራ ከጫካ ለቅመው አስረው እንዲደርቅም ያስቀምጣሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት የሚያደርገው ጥረት በዓሉ በስኬትና በድምቀት እንዲከበር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በዚህም ያሆዴ ከተናጠል ይልቅ ትብብርን የሚያጠናክር ነው ማለት ይቻላል። እሴቱ በትብብር መድመቅ እንደሚቻልም የሚያሳይ ነው። ይህን ሀሳብ የሚጋሩት አቶ መስፍን የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል በምንም ሁኔታ መነጣጠል የማይቻል ትስስርን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ። ሀገራዊ አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር ዘመናትን የተሻገረና ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ባህላዊ እሴት ያለው መሆኑንም ይናገራሉ። በዓሉ ሊከበር ጥቂት ቀናት ሲቀረው አባውራዎች በቅርጫ ማህበራቸው አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ የእርድ በሬ ይገዛሉ። በዚህ ወቅት ገንዘብ ማዋጣት ያልቻሉ የቅርጫ አባላት እህል በሚደርስበት ወቅት ለመክፈል ተስማምተው በሬውን በዱቤ እንዲገዙ ይደረጋል፡፡ ይሄም የሚሆነው በያሆዴ በዓል አንዱ ሲበላ ሌላው ተመልካች መሆን ስለሌለበት ነው። እርስ በርስ መጨካከን እንዳይኖርና በዓሉን በአብሮነት ሁሉም ተደስቶ ማክበር እንዲችል ለማድረግ ነው። ከበዓሉ ዕለት በፊት ያለው የመጨረሻ ገበያም የእብድ ገበያ (መቻዕል ሜራ) የሚል ስያሜ አለው። ይሄ ሥያሜ ያገኘው በዓሉ ሲቃረብ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ውጥረት ታሳቢ በማድርግ ነው፡፡ በዚህ የእብድ ገበያ ህብረተሰቡ መገበያየት የሚጀምረው ጠዋት ማለዳ ጀምር ሲሆን የግብይት ሂደቱ የሚጠናቀቀው ደግሞ እኩለ ቀን ላይ ነው፡፡ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለመግዛትና የያሆዴ በዓል ከተከበረ በኋላ ለአንድ ወር ገበያ ስለማይቆም ይህን ታሳቢ ያደረገ ግብይት ለመፈጸም የግብይት ሂደቱ ጥድፊያ የበዛበት ሆኖ ይታያል። ያሆዴ በዓል መከበር የሚጀምረው በአተካን ሂሞ ወይም በአተካና ምሽት ሲሆን ይህም ከበዓሉ አንድ ቀን በፊት ያለው ምሽት ነው። ስያሜውን ያገኘው "አተካና" ከተሰኘና በያሆዴዎች ዘንድ ለክብር እንግዳ እና በዘመን መለወጫ ከሚዘጋጅ ምግብ ነው። አተካና ከወተት፣ ከአይብ፣ ከቡላ፣ ከቅቤና ከሌሎች የቅመማ ቅመም ውጤቶች የሚዘጋጅ ምግብ ሲሆን በጣም ጣፋጭና የምግበ ፍላጎትን የሚጨምር ምግብ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ይሄንን የተለየ ምግብ ተሰባስቦ በአብሮነት በመመገብ በደመቀ መልኩ በዓሉን ማክበር ይጀምራል፡፡ የአካባቢው አባቶች በወጣቶች የተዘጋጀ የማቀጣጠያ እንጨት (ሳቴ) ይዘው ትልቅ በሚባሉ አባውራ ቤት ደጃፍ ወደ ተዘጋጀው የችቦ ደመራ (ጦምቦራ) ቦታ ይመጣሉ:: የሀገር ሽማግሌች አዲሱ ዓመት የብርሃን ዓመት እንዲሆን፤ ለሀገርና ለህዝቦቿ ሰላም እንዲጸና፤ አብሮነት እንዲጠናከር፣ ሰላምና ፍቅር እንዲነግስ ፈጣሪያቸውን ከተማጸኑ በኋላ ችቦውን በእሳት ይለኩሳሉ፡፡ ችቦው ከተለኮሰ በኋላ የአካባቢው ወጣቶች ተሰባስበው ያሆዴ …ያሆዴ! …ያሆዴ! በማለት እየጨፈሩ ያነጋሉ ይጨፍራሉ:: በሀድያዎች ዘንድ "ያሆ" ማለት የአዲስ ዓመት መግባትን ተከትሎ ማብሰሪያ ጭፈራ ሲሆን "ኤዴ" ማለት ደግሞ አገናኝ ማለት ነው፡፡ በያሆዴ በዓል የእርድ ሥነ ስርዓት ለማከናወን ነዋሪዎች የሚሰበሰቡበት ስፍራ "ነፈራ" የሚል ስያሜ አለው። የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሰፋ ያለ ቦታ ሰሆን በተለያዩ የጥላ ዛፎች የተዋበና ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀም ነው። በእለቱ ለእርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኋላ የባህል ሽማግሌዎች የበሬውን ሻኛ በሰርዶ ሳር ለጋ ቅቤ ይቀባሉ፤ ወተትም ያፋሱበታል፡፡ ይህ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ጋቢማ የሚባል ሲሆን (የመልካም ምኞት) መግለጫ ስነ ስርዓትም ነው፡፡ ይህም ሥነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም "ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሀገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን " እያሉ በአባቶች ምርቃት ከተካሄደ በኋላ የእርድ ስነ ስርዓት ይከናወናል፡፡ የእርድ ሥነ ስርዓቱ የተከናወነበት ቤት እማወራ አስቀድመው ባደረጉት ዝግጅት መሰረት ቅቤ፤ (ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ) እንዲሁም ከታረደው የበሬ ሥጋ አርዚ ማራ (ቅምሻ) ይወሰድና ክትፎ ከተዘጋጀ በኋላ በጋራ እየበሉ እየተጫወቱ ይውላሉ፡፡ በዚህም በቅርጫ ሥጋው ላይ ከሚሳተፉት የቤተሰብ አባላት ውጪ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችም ጭምር አብረው በመብላት በመጠጣት በዓሉን በአንድነት ያሳልፋሉ፡፡ ቀሪውን የቅርጫ ሥጋም አባላቱ ተከፋፍለው ወደ እየቤታቸው ይወስዱታል፡፡ በዓሉ አብሮ የመብላት፣ የመጠጣት፣ የመጠያየቅ፣ ችግርንና ግጭትን በጋራ ተወያይቶ የመፍታት፣ መፈቃቀርና መተሳሰብን የሚፈጥር፣ አቅመ ደካሞችና የተቸገሩ የሚረዱበት የአብሮነት መገለጫ በመሆኑ በተለየ መልኩ ይከበራል፡ ከእርድ ሥርዓቱ በኋላ በማግስቱ ልጆች አደይ አበባ (ዘራሮ) ይዘው ወደ ወላጆቻቸው እየጨፈሩ ይመጣሉ። የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባላሉ። ከስጋውም፣ ከቦርዴውም፣ ከአተካናውም እንዲመገቡ ያደረጋል። ይህ ስነ ስርዓትም ሚክራ ይባላል። በያሆዴ የዘመን መለወጫ በዓል ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ሥጋና አደይ አበባ ጭምር ይዘው ይሄዳሉ። በዓሉ ያላገቡ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ለአዲስ ህይወት ጅማሬ የሚያበስሩበት በመሆኑን የተለየ ድባብ አለው፡፡ የያሆዴ በዓል ካሉት እሴቶች አንዱ የህብረተሰቡን የአካባቢ ልማት ተሳትፎ ማበረታታት ተጠቃሽ መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ዕሴቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናቅቀው ለማህበረሰብ ጥቅም እንዲውሉ ጭምር አቅም እየሆነ መምጣቱን ነው የሚናገሩት።ይህ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የማህበራዊ መስተጋብር መጋመጃ የሆነው በዓል እሴቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል መስራት ይገባል። እሳቸው እንዳሉት በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማስቻል እየተሰራ ነው፡፡ ለዚህም መምሪያው ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ዕሴቱን የመሰነድና ምርምሮች ማካሄድን ጨምሮ እያከናወናቸው ያሉ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1015
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1744
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2552
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2702
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 333
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 321
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6176
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4656
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ኢሬቻ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ማንሰራራት!
Oct 3, 2025 799
ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ሰዎች በክረምት ወቅት ከሚከሰት መለያየትና መራራቅ በኋላ ዳግም የሚገናኙበት፣ በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት ዕለት ነው። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። ኢሬቻ የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ጥብቅ ቁርኝት የሚገለጽበት የገዳ ስርዓት አንዱ አካል ነው፡፡ የኢሬቻ እሴቶች ጠንካራ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ያላት ሀገር ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው። አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ አብሮነት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ዕርቅ እና ሌሎችም ተጠቃሽ የመልካም እሴቶች መገለጫ ነው። በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አንዱ እሴት ኢሬቻ ሲሆን፤ ለሀገር ማንሠራራትና ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሠረት ይሆናል፡፡ ኢሬቻ አብሮነት የሚጸናበት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ይበልጥ የሚጎላበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጎለብትበት፣ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ማሰሪያ ከፍ ያለ በዓል ነው፡፡ ኢሬቻ በጋራ የሚያከብሩትና የዓለም ቱሪስቶች የሚታደሙበት ሲሆን፤ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል አከባበር ሀገራዊ ማንሰራራት በተግባር የተረጋገጠበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ዓለም የኢትዮጵያን መቻል በተግባር ባየበትና ሌሎች ለሀገር ማንሰራራት ዕውን መሆን መሠረት የሚጥሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኘሮጀክቶች ይፋ በተደረጉበት ማግስት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡ በዓሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመላው ኢትዮጵያዊያንን ሕብረት የሚንጸባረቅበት ሆኖ በተለያዩ አከባቢዎች በድምቀት እየተከበረም ይገኛል፡፡ በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Waaqa Uumaa, Waaqa Uumamaa ፍጥረትን የፈጠርክ ፈጣሪ Gurraacha garaa garbaa የእውነትና የሰላም አምላክ! Dogoggora nu oolchi ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! Dacheef nagaa kenni ለምድራችን ሰላም ስጥ! Laggeenif nagaa kenni ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! Olota keenyaaf nagaa kenni ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! . . . Loowan keenyaaf nagaa kenni " ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "አሜን! አሜን! አሜን!” ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 25 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ " ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት " በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" Irreecha Birraa (በውኃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን፤ በዓመቱ አጋማሽ ላይ "ኢሬቻ ቱሉ" Irreecha Arfaasaa ደግሞ በተራራማ ቦታ ይከበራል። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ነው። የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመምጣቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ይህ ከማህበራዊ መስተጋብር አኳያም ሰዎች የሚሰባሰቡበትና የሚገናኙበት ነው። ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ብርሃን (ብራ) ስለደረሰ ለዚያ ምልክት ይሆን ዘንድ የለመለመ እርጥብ ሣር ይዘው ወደ ወንዝ በመውረድ ንጹህ ውሃ ውስጥ እየነከሩና እየረጩ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ አብሮነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። ኢሬቻ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው "ዋቃ" "Waaqa" ምስጋናውን ለማድረስ የሚከበር ሲሆን፤ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲከበር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። ኢሬቻ የወንድማማችነትና የአንድነት አርማ ሲሆን፤ የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ፣ የህብረ ብሔራዊ አብሮነት ማስተሳሰሪያም ጭምር ነው፡፡ በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይበዛል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል፣ አንድነት ይጸናል። ኢሬቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ነው። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ስለሆነም ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር እንዲህ እያሉ ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። የበዓሉ ታዳሚዎች ከዋዜማው ጀምሮ በሆረ ፊንፊኔና በሆረ ሀርሰዲ በመሰባሰብ፤ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎችን በማዜምና ምስጋና በማቅረብ አድረው በነጋታው ዋናውን የምስጋና በዓልም ያከናውናሉ፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የደስታና የምስጋና ምልክት የሆነውን ባህላዊ ነጫጭ ልብስ ለብሰው፣ ባህልን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ሁነቶችን በመከወን ልዩ ልዩ ዜማዎችን በማዜም፣ ግጥሞችን በማቅረብ፣ ወደ ፈጣሪ በመጸለይ እና ምስጋና በማቅረብ ሥርዓቱን ያከናውናሉ፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ከማቀራረብና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጾኦ ያለው ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገር የመጡ ልዑካን በበዓሉ ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። የኢሬቻ በዓል ለቱሪዝም ፍሰት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ጉልህ ነው፤ በርካታ የባህር ማዶ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የሚታደሙበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ ሲሆን፤ ዘርፉን በማጠናከር እና ብሔራዊ ልማትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚናንም የሚጫወት ነው፡፡ ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!
በትግራይ ክልል የመስቀል በዓል አከባበር
Sep 27, 2025 809
የመስቀል በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በልዩ ድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ ነው። በዓሉ እንደየአካባቢው ባህላዊና ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል። በትግራይ ክልልም የመስቀል በዓል እንደሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሁሉ በናፍቆት ከሚጠበቁና በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት ተርታ ይመደባል። ለዚህም ሲባል የተለያዩ ዝግጅቶች ከበዓሉ ዋዜማ በፊት እንዲጠናቀቁ የሚደረግ ሲሆን፥ በተለይ በየዓመቱ መስከረም 16 እና 17 ዘመድ አዝማድ ተጠራርተው የሚገናኙበት የፍቅርና የአብሮነት በዓል ሆኖ ይከበራል። የክርስቶስ ግማደ መስቀል በንግስት ኢሌኒ አማካኝነት መገኘቱን በማሰብ በየዓመቱ መስከረም አጋማሽ ላይ የሚከበረው የመስቀል በዓል የመስቀል ኃያልነት፣ እውነት በተደበቀበት ለዘላለም እንደማይቀርና ፍቅርን አብዝቶ የሚሰበክበት ከዚህ ባለፈም እርቅ የሚወርድበትና ደስታ የሚገለጽበት አጋጣሚ መሆኑም ይገለጻል። በትግራይ የበዓሉን ታላቅነትና ክብር ለማድመቅ ምእመናን ጽዱ ልብስ ለብሰውና የተለያዩ ዝማሬዎችን በማሰማት ደመራ ወደሚደመርበት ሥፍራ ችቦ ይዘው በመሄድ ደምራውን በማቀጣጠል የሚያከበሩት ሲሆን፣ በእለቱ የቤት እንስሳት ጭምር ቀንዳቸውና ጀርባቸው ላይ ቅቤ ተቀብተው እንዲያርፉ ይደረጋል። ዘመድ አዝማድ፣ ጎረቤታሞች፣ አብሮ አደጎችና የበዓሉ ታዳሚ እንግዶችም ተሰባስበው ማለዳ ላይ ገንፎ በማዘጋጀት ይመገባሉ። የእንስሳት እርድ በማከናወን ባህላዊ መጠጦችን በማዘጋጀት በዓሉን የፍቅር፣ የመሰባሰብ፣ የአንድነትና ተካፍሎ የመብላት በዓል መሆኑን በተግባር የሚያሳይበት ክስተት ሆኖ ያልፋል። "ዓኾይ ዓኾኾይ" የጎመን ምንቸት ውጣ የገንፎ ምንቸት ግባ በማለትም ችቦ ተሎኮሶ በየቤቱ በመዞር የምረቃ እና ለሚቀጥለው ዓመትም በሰላምና ደስታ እንዲሁም እድሜና ጤናን በመመኘት ይከወናል። የአደባባይ በዓል የሆነው የመስቀል በዓል በዝማሬ፣ በሆታና እልልታ የሚገለጽ ሲሆን፤ ወርሃ መስከረም እሸት አሽቶ አበቦች አብበውና ምድር ልዩ ልምላሜን ተላብሶ የሚታይ በመሆኑ ልክ በታሪኩ እንደሰፈረው የሰላም፣ የእውነትና የአንድነት በዓል መሆኑን በተግባር የሚታይበት ነው።