አራተኛ ቀኑን የያዘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዝግጅት - ኢዜአ አማርኛ
አራተኛ ቀኑን የያዘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዝግጅት
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዋን ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር ታደርጋለች።
ለማጣሪያው በአሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ከመጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ዝግጅታችውን ማድረግ ቀጥለዋል።
ቡድኑ የአራተኛ ቀን ልምምዱን ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ማድረጉን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
ጋቶች ፓኖም (አል ዓረቢ ሳዑዲ ዓረቢያ) እና ከነዓን ማርክነህ ( አል ሻባብ ኦማን) ብሔራዊ ቡድኑን በመቀላቀል ልምምድ ማድረግ ጀምረዋል።
ኢትዮጵያ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር የማጣሪያ ጨዋታዎቿን መጋቢት 18 እና 22 ቀን 2018 ዓ.ም ታደርጋለች።