ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የተመዘገበው ውጤት ለዘርፉ ትኩረት ከተሰጠ የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካት እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ ነው
Oct 28, 2025 29
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦በአገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው ውጤት ለዘርፉ ትኩረት ከተሰጠ የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካት እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ በ2017 ዓ.ም አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት ተሰጠ። ሽልማቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለተማሪዎቹ አስረክበዋል።   ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማዋ ከፍተኛ ውጤት ከተመዘገበባቸው ዘርፎች መካከል ትምህርት አንዱ ነው። መንግስት የትምህርት ስብራትን ለመጠገን አዲስ ፖሊሲና ሥርዓተ ትምህርት በመቅረጽ ተግባራዊ ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። የመማር ማስተማር ሥርዓቱን ምቹ የማድረግና የትምህርት ግብዓቶችን የማሟላት ሥራ በስፋት ሲሠራ መቆየቱን ገልጸው፤ በዚህም የተማሪዎች ውጤት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እና እያደገ መምጣቱን አመልክተዋል። በአገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው ውጤት ለዘርፉ ትኩረት ከተሰጠ የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካት እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።   በቀጣይ የመጣውን ውጤት እያበረታታን ለሌላ ስኬት ጠንክረን የምንሠራ ይሆናል ነው ያሉት። ተማሪዎች ዛሬ የተሰጣቸው ሽልማት በቀጣይ ሕይወታቸው ጠንክረው በመስራት ለአገራቸው የበኩላቸውን የላቀ ድርሻ እንዲያበረክቱ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።   ዛሬ በተሰጠው እውቅና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው ታብሌት ኮምፒውተር ተበርክቶላቸዋል። እንዲሁም ለመጣው ውጤት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና የትምህርት ማኅበረሰብ እውቅና ተሰጥቷል።
አፍሪካ የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ለመሙላት በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር ፈሰስ ማድረግ አለባት - የአፍሪካ ህብረት
Oct 28, 2025 38
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፦ አፍሪካ የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ለመሙላት በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እንደሚገባት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ በአንጎላ ሉዋንዳ ተጀምሯል። በጉባኤው መክፈቻ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የአፍሪካ ሀገራትና መንግስታት መሪዎችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር አፍሪካ የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ለመሙላት በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እንደሚገባት ገልጸዋል። መሰረተ ልማት የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የጀርባ አጥንትና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ የመሰረተ ልማት ፕሮግራም(ፒዳ) በአህጉሪቱ 16ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ እና አራት ሺህ ኪሎ ሜትር የባቡር መንገድ ግንባታ መከናወኑን ጠቁመው 30 ሚሊዮን ዜጎች ኢነርጂ ተደራሽ ማድረጉን አመልክተዋል። በሀገር በቀል የሀብት ማሰባሰብ፣ በአማራጭ ፋይናንስና በጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት አማካኝነት በቀጣይ ምዕራፍ የፕሮግራሙን ስኬታማነት የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰራ ተናግረዋል። የአፍሪካ የትስስር አጀንዳ ራዕይ ብቻ ሳይሆን የአህጉሪቱ ስኬቶች በተግባር የሚረጋገጥበት መንገድ ጭምርም ነው ብለዋል። የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ ጉባኤው በአፍሪካ የሚገነቡ ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክቶች ሀብት የማሳባሰብና አፈጻጸም ደረጃ የሚገመገምበት መሆኑን አመልክተዋል። ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ እስከ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚቆይ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጥራትና ጊዜ እንዲጠናቀቁ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል ይደረጋል
Oct 28, 2025 39
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን ከበለጸጉ ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ መሰረት የሚጥሉ ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጥራትና የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን አጠናቃ ባስመረቀችበት ማግስት የጉባ ብስራቶች የሆኑ የ30 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ይፋ አድርጋለች፡፡ እነዚህ ፕሮጀክቶች የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ግንባታ፣ የኒውክሌር ሀይል ማበልጸጊያ፣ የጋዝ ማምረት፣ የነዳጅ ማጣሪያ እና በስድስት ዓመታት ውስጥ ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ ቤቶች ግንባታ ናቸው፡፡ ፕሮጀክቶቹ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠርና የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት ለሕዝቡ የመልማት ፍላጎት ምላሽ የሚሰጡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ሀገራዊ ፕሮጀክቶቹ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በመሰረታዊነት የሚቀይሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል መብራቱ መለስ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ ትላልቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡   ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶቹ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሽግግር የሚያፋጥኑ ወሳኝ ርምጃዎች መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡ ሌላው የምክር ቤት አባል አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) ፕሮጀክቶቹ ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ስሟ በድህነት ሲጠቀስ የነበረበትን የታሪክ ምዕራፍ የሚቋጩ እና በሌላ ገጽታ የሚያስተዋውቁ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡   ግንባታቸው የተጀመሩና በሂደት ላይ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያን ካደጉ ሀገራት ተርታ የሚያሰልፉ መሆናቸውን ገልጸው፤ የኢትዮጵያን በጎ ገጽታም ይገነባሉ ብለዋል፡፡ ሌላዋ የምክር ቤት አባል አዲሷ አሰፋ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለአፍሪካ ትሩፋት የሚሆኑ የልማት ፕሮጀክቶችን እውን ማድረጓን ገልጸዋል፡፡   ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉም አረጋግጠዋል፡፡ የምክር ቤት አባላቱ ምክር ቤቱ በህገ መንግስቱ በተሰጠው ስልጣን መሰረት የፕሮጀክቶችን ገቢራዊነት ይከታተላል ብለዋል፡፡
የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ያሳድጋል 
Oct 28, 2025 40
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ፋይዳው የጎላ መሆኑን በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። በቅርቡ ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት ከሀይል አማራጭነት የዘለለ የተለያዩ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ከእነዚህ ጠቀሜታዎች መካከል አንዱ የኒኩሌር ህክምና አገልግሎት ይገኝበታል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መምህር፣ ሀኪም፣ ተመራማሪና የካንሰር ሕክምና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን ሁነኛው ለኢዜአ እንደገለፁት የኒኩሌር ፕላንቱ በሕክምናው ዘርፍ ለኢትዮጵያ ትልቅ እድል ይዞ የሚመጣ ነው። በተለይ በዋናነት የካንሰር በሽታን ለማከም ያለው ፋይዳ ላቅ ያለ በመሆኑ የህክምና አገልግሎቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደርሰዋል ብለዋል። አክለውም ለራዲዮ ቴራፒ ሕክምና የሚውሉ መድሀኒቶችን ለማምረትና የቆይታ ጊዜያቸው ከስምንት ቀን የማይበልጡ መድሀኒቶችን ብልሽት መፍታት ያስችላል ነው ያሉት። ከኒኩሌር ጋር በተያያዘ መንግስት የወሰደው ኢንሼቲቭ ከህክምና አገልግሎቱ ባለፈ በዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያለው ፋይዳም ከፍተኛ በመሆኑ መበረታታት እንዳለበት ዶክተር ሰለሞን ተናግረዋል።   ሌላው የዩኒቨርሲቲው መምህርና የህጻናት ካንሰር ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሙሉአለም ንጉሴ በበኩላቸው ያደጉ ሀገሮች የኒኩሌር ሕክምናን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠቀሙበት አንስተዋል። የኒኩሌር ሀይል ለአዋቂም ሆነ ለሕጻናት ሕክምና የበሽታውን ሁኔታና ያለበትን ደረጃ ለይቶ ለማከም ያለው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ፕሮጀክቱ ለሕክምናው ዘርፍ ጭምር ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ብለዋል። የኒኩሌር ሀይል ለካንሰር ሕክምና አገልግሎት ሦስት ዋና ዋና ፋይዳ አለው ያሉት ባለሙያው የካንሰር አይነቱንና የስርጭቱን መጠን እንዲያውቅ ይረዳዋል ነው ያሉት። ሕመምተኛውም የበሽታው አይነትና ስርጭትን መሰረት ያደረገ ሕክምና እንዲያገኝ እንደሚያስችለው ገልጸዋል። ለካንሰር ሕሙማን የኒኩሌር ሕክምና በሀገር ውስጥ ስለማይሰጥ ሕክምናውን ለማግኘት ወደ ውጪ እንደሚላኩ የገለጹት ዶክተር ሙሉአለም በዚህም ምክንያት ለወጪና እንግልት ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል።   የኒኩሌር ሕክምና ከሌሎቹ የሲቲ ስካን፣ ኤም አር አይ እና ሌሎች መሳሪያዎች አንጻር ያለውን በሽታ ለይቶ ማሳየት ብቻ ሳይሆን ያደረሰውን የጉዳት መጠን ጭምር ለይቶ የሚያሳይ ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የሕክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ክብሩ ክፍሌ ናቸው። በካንሰር የተጠቃ የሰውነት አካል ምን ያህል እንደተጎዳ፣ የትኛው ክፍሉ ሥራውን በአግባቡ እያከናወነ እንደሚገኝ የሚለውን በትክክል መለየት የሚያስችል የዘመናዊ ሕክምና ትልቅ መሳሪያ መሆኑን አስረድተዋል። እንደ ሀገር ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ከፍ ወዳለ ደረጃ የሚያሸጋግር በመሆኑ መንግስት የወሰደው ተነሳሽነት ሊበረታታና ሊደገፍ ይገባል ሲሉም ምሁራኑ ገልፀዋል።
የሚታይ
አፍሪካ የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ለመሙላት በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር ፈሰስ ማድረግ አለባት - የአፍሪካ ህብረት
Oct 28, 2025 38
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፦ አፍሪካ የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ለመሙላት በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እንደሚገባት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ በአንጎላ ሉዋንዳ ተጀምሯል። በጉባኤው መክፈቻ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የአፍሪካ ሀገራትና መንግስታት መሪዎችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር አፍሪካ የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ለመሙላት በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እንደሚገባት ገልጸዋል። መሰረተ ልማት የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የጀርባ አጥንትና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ የመሰረተ ልማት ፕሮግራም(ፒዳ) በአህጉሪቱ 16ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ እና አራት ሺህ ኪሎ ሜትር የባቡር መንገድ ግንባታ መከናወኑን ጠቁመው 30 ሚሊዮን ዜጎች ኢነርጂ ተደራሽ ማድረጉን አመልክተዋል። በሀገር በቀል የሀብት ማሰባሰብ፣ በአማራጭ ፋይናንስና በጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት አማካኝነት በቀጣይ ምዕራፍ የፕሮግራሙን ስኬታማነት የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰራ ተናግረዋል። የአፍሪካ የትስስር አጀንዳ ራዕይ ብቻ ሳይሆን የአህጉሪቱ ስኬቶች በተግባር የሚረጋገጥበት መንገድ ጭምርም ነው ብለዋል። የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ ጉባኤው በአፍሪካ የሚገነቡ ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክቶች ሀብት የማሳባሰብና አፈጻጸም ደረጃ የሚገመገምበት መሆኑን አመልክተዋል። ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ እስከ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚቆይ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ  የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ የበኩላችንን እየተወጣን ነው - የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት
Oct 28, 2025 52
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በሰላማዊ፣ በሰጥቶ መቀበልና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል።   በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ቀይ ባህርን እንድታጣ ያደረገውን ውሳኔ ማን ወሰነ ብለን ስንፈልግ ተቋማት አልገቡበትም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም ብለዋል።   ኢዜአ ያነጋገራቸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፍትሃዊ፣ ምክንያታዊና የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክር ቤት አባል አቶ ሳዲቅ አደም እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዓለም አቀፍ የሕግ ማዕቀፍና በተለያዩ ኮንቬንሽኖች ተቀባይነት ያለው ነው ።   ኢትዮጵያ ከባህር በር ርቃ የቆየችበት መንገድ ተገቢ አለመሆኑን ጠቁመው፤ የኢትዮጵያ ጥያቄ የሰጥቶ መቀበል መርህን እና ሰላማዊ መንገድን ያስቀደመ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ስኬታማ እንዲሆን ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ አሳስበው፤ ምክር ቤቱም አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ ላይ መሆኑን ተናግረዋል። የምክር ቤት አባል አስቴር ከፍታው በበኩላቸው፤ የባህር በር ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል፡፡   ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚ መሆን የምትፈልገው በሰላማዊ መንገድ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህ ስኬት የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ መላው ሕዝብ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በፍጥነት እያደገ በመምጣቱ የባህር በር ይህንኑ ፍላጎት ለማሳካት መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤት አባል አምባሳደር ተውፊቅ አብዱላሂ (ዲ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የመላው ሕዝብ አጀንዳ መሆኑን ተናግረው፣ አጀንዳው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚነት ጥያቄ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተመሰረት መሆኑን ጠቁመው፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት አለበት ብለዋል። ፍትሐዊ የሆነው ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ አስፈላጊውን ሁሉ በማድረግ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ 63 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች የጤና መድህን ተጠቃሚ ሆነዋል
Oct 28, 2025 81
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ 63 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች በጤና መድህን ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ውስጥ የጤና መሰረተ ልማቶችን ለማስፋት እየተሰራ ነው። በኢትዮጵያ 63 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች በጤና መድህን ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህም በርካታ ዜጎች የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረጉን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል። የመድሃኒት አቅርቦትን በተመለከተ ከውጭ የሚገቡ መድሃኒቶች ለመቀነስና በአገር ምርቶች ለመተካት ሙከራ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የጤናውን ዘርፍ ለማስፋትና የህዝቦችን የጤና አገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። ለአብነትም የቅዱስ ጵውሎስ ሆስፒታል አንድ ሺህ አልጋ ያለው የመሰረተ ልማት ግንባታ ማደረጉን ገልጸው፤በቀጣይ አስፈላጊው ግብዓት ተሟልቶ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረግ ገልጸዋል።
የትምህርት ጥራትን የሚያሻሽሉና ትውልድን የሚገነቡ ስራዎች በስፋት እየተሰሩ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 28, 2025 73
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን የሚያሻሽሉና ትውልድን የሚገነቡ ስራዎች በስፋት እየተሰሩ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ በተካሄደው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው እንድገለጹት፤ የትምህርቱን ጥራት ለማስጠበቅ ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ ትውልድን የሚገነቡና የሚያንጹ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው። ከእነዚህ መካከልም በትምህርት ተቋማት አካባቢ የሚገኙ አዋኪ ድርጊቶችን የማጥራት እንዲሁም በትምህርት ለትውልድ ፕሮጀክት የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ለመምህራን የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ከመስጠት ባሻገር በትምህርትና በፈተና አሰጣጥ ላይ ለውጥ እንዲመጣ መደረጉን ገልጸዋል። በትምህርት ቤት አካባቢዎችም የስፖርት ማዘውተሪያና የመዝናኛ ስፍራዎችን በመገንባት ጤናማ ትውልድ መገንባት መጀመሩን ነው የተናገሩት። በዘንድሮው የትምህርት ዘመንም ከ43 ሚሊየን በላይ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የመማሪያ መጻሕፍት መታደሉንና ይህም የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ከተሰሩ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆኑን ገልፀዋል። የተማሪዎች ምገባን በተመለከተም አስደናቂና ማሕበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስራዎች በመስራት ሁሉም የሚመኛት ኢትዮጵያ እንድትሆን እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።
የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው 
Oct 28, 2025 103
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፣ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊ (ጂኦግራፊያዊ)፣ ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት 30 ዓመት በላይ የወሰደ ትግል እንደነበር ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አገሪቷ ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ 30 ዓመት አያስፈልጋትም ብለዋል። ይህን ጉዳይ ለመፍታት በተረጋጋ፣ በሰከነ እና በውይይት መሄድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ "ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅብንም" ሲሉ በአጽንኦት ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልወሰነው፣ ተወካዮች ያላዩትና ካቢኔም ያልወሰነው ውሳኔ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ትልቅ ጉዳይ ማን ወሰነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ህጋዊ እና ተቋማዊ መሠረት የሌለው ነው ብለዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በየተቋማችን የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ እንተጋለን  - የመንግስት ሠራተኞች
Oct 28, 2025 51
ጎንደር/ ገንዳ ውሃ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡- በሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፏቸውን በማጎልበት በየተቋማቸው የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ በትጋት እንደሚሰሩ በጎንደር ከተማ የመንግስት ሠራተኞች ገለጹ። ሠራተኞቹ "የውጭ ባንዳዎችንና የውስጥ ባንዳዎችን ቅዠት በማምከን አንፀባራቂ ድሎችን እናስመዘግባለን " በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊ ሠራተኞቹ እንዳሉት፤ አገልግሎት አሠጣጥን በማዘመን ቀልጣፋና ፈጣን ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ይሰራሉ።   ከተሳታፊዎቹ መካከል አስካል ፀሐይ በሰጡት አስተያየት፤ የመንግስት ተቋማትን የአገልግሎት አሠጣጥ ለማዘመን የተጀመሩ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራሮች የተገልጋዩን እንግልትና ቅሬታ የሚፈታ መሆኑን አንስተዋል። ይህም የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ከመሰረቱ የሚፈታና ሠራተኛውም በተመደበበት መስክ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ምቹ የስራ ምህዳር የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ ሌላኛው ተሳታፊ መልካሙ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሠራተኛውን የስራ ተነሳሽነት የሚያጎለብትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እውቀቱንም ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት በተመረጡ ተቋማት የጀመራቸው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ ወደ ሁሉም ተቋማት እንዲሠፉ የሚደግፉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዲጂታል ቴክኖሎጂው የተገልጋዩን ጊዜ ፣ገንዘብንና ጉልበትን ቆጥቦ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ያሉት ደግሞ አቶ ባዘዘው ታምራት ናቸው፡፡ ሠራተኞቹ በሰላም ግንባታ ላይ ሲያደርጉ የቆዩትን ተሳትፎ በማጎልበት በየተቋማቸው የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ በታማኝነትና በቅንነት ተግተው እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሲርቪስና የሰው ሃብት ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ነጻነት መንግስቴ እንደገለጹት፤ መሶብ የአንድ ማዕከልን ጨምሮ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋና ፈጣን ማድረግ የሚያስችል ነው፡፡   በመንግስት ለሠራተኛው የተደረገው የደመወዝ ማሻሻያ የስራ ተነሳሽነቱን የሚያጎለብት በመሆኑ ሠራተኛው በሠላም ግንባታና በልማት እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክር አሳስበዋል፡፡ በተመሳሳይ የምዕራብ ጎንደር ዞን የመንግስት ሠራተኞች ውይይት አካሄደዋል።   በገንዳውሃ በተካሄደው ውይይት ከተሳተፉት ሠራተኞች መካከል ዮሐንስ ዓለሙ የውጭና የውስጥ ጠላቶችን ሴራ በአንድነት በማክሸፍ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ሌላው ተሳታፊ ግርማ ሰፊው ፤ ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባሻገር አፍራሽ አጀንዳዎችን ቀድሞ በመገንዘብ ለመመከት ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ አቋም በመያዝ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ የተናገሩት ደግሞ አትጠገብ አሻግሬ ናቸው።   የዞኑ ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ቢተው አሳየ በበኩላቸው፤ ነጠላ ትርክትን በማስወገድ ሀገሪቱ የያዘችውን የእድገት ጎዳና ማስቀጠልና ሰላምን ማፅናት ከሁሉም የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን አብራርተዋል። የመንግሥት ሠራተኛው ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት በመስጠት የሕብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ መትጋት እንዳለበት አሳስበዋል።
በሐረሪ ክልል የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ይጠናከራሉ
Oct 28, 2025 75
ሐረር ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በትኩረት ሊከናወኑ በሚገባቸው ተግባራት ዙሪያ ለክልሉ አመራር አባላት አቅጣጫ ሰጥተዋል። በወቅቱም ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።   ህገወጥ የመሬት ወረራና የቤት ግንባታ እንዲሁም ህገ ወጥ ንግድን የመከላከሉና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ተግባር በአመራሩ በትኩረት ሊከናወኑ ከሚገባቸው ተግባራት መካከል እንደሆኑም ጠቅሰዋል። በክልሉ በአሁኑ ወቅት የተጀመሩና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ሰፋፊ የልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት የማብቃት ስራ ላይ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። እንዲሁም በኮሪደር ልማት የተጀመሩ ስራዎች በተያዘላቸው ጊዜ ገደብ የማጠናቀቅ ስራን ማከናወን ይገባል ሲሉም አክለዋል። በበጀት ዓመቱ አዲስ በዕቅድ የተያዙ የወንዝ ዳርቻ ልማትና ሌሎች ስራዎችን በፍጥነት ወደ ስራ የማስገባት ተግባር ይከናወናል ብለዋል።   ከዚህም በተጨማሪ የገጠሩን ማህበረሰብ ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ በምርት አሰባሰብ ወቅት የምርት ብክነት እንዳይከሰት በማድረግ አርሶ አደሩ ምርቱን ለገበያ እስኪያቀርብ ድረስ ክትትል እና ድጋፍ ይደረጋል ሲሉም አክለዋል። በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ የመሰብሰብ ስራን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ተናግረዋል። ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ለማህበረሰቡ የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ስራን ማሳለጥ እንደሚገባም አመልክተዋል።  
የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው 
Oct 28, 2025 103
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፣ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊ (ጂኦግራፊያዊ)፣ ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት 30 ዓመት በላይ የወሰደ ትግል እንደነበር ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አገሪቷ ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ 30 ዓመት አያስፈልጋትም ብለዋል። ይህን ጉዳይ ለመፍታት በተረጋጋ፣ በሰከነ እና በውይይት መሄድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ "ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅብንም" ሲሉ በአጽንኦት ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልወሰነው፣ ተወካዮች ያላዩትና ካቢኔም ያልወሰነው ውሳኔ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ትልቅ ጉዳይ ማን ወሰነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ህጋዊ እና ተቋማዊ መሠረት የሌለው ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን በተከተለ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችውን ጥረት እንደግፋለን-የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Oct 28, 2025 110
ወላይታ ሶዶ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን ተከትላ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ በቁርጠኝነት እንደሚደግፉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ኢትዮጵያ ለዘመናት ስትጠቀመው የቆየው የባህር በር በታሪክ አጋጣሚ ከእጇ ወጥቶ ከወደብ አልባ ሀገራት ተርታ ተሰልፋ ቆይታለች። መንግስትም የኢትዮጵያዊያን የዘመናት ቁጭት ሆኖ የቆየውን የባህር በር ጥያቄ በይፋ በማንሳት በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል። ይህንንም የኢፌድሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮችና በፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ የመክፈቻ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር አጽንኦት መስጠታቸው የሚታወስ ነው። በጉዳዩ ላይ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት የባህር በር ጥያቄው የትውልዱ የዘመናት ቁጭትን የሚመልስ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ መንግስት የጀመረው ጥረት እንዲሳካ በቁርጠኝነት እንደሚደግፉ ተናግረዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ጎበዜ አበራ የባህር በር ለሀገር ሁለንተናዊ ልማትና ዕድገት መሰረት መሆኑን አንስተዋል።   ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን በተከተለና ዲፕሎማሲየዊ በሆነ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት እንዲሳካም ምክር ቤቱ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። "ኢትዮጵያ ለዘመናት ስትጠቀምበት የነበረውን የባህር በር ማጣቷ ለድህነታችን አንድ ምክንያት ከመሆኑ በላይ የሚያስቆጭ ነው" ያሉት ደግሞ የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ አቶ ተፈራ ጎበና ናቸው።   የባህር በር ጥያቄን ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶችን ማጠናከር ለድርድር መቅረብ የለበትም ያሉት አቶ ተፈራ የጉዳዩ መሳካት ልማትና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ለማፋጠን አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። የባህር በር ለማግኘት መንግስት የጀመረው ተግባር ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ እውን እንዲሆን ፓርቲያቸው የሚጠበቅበትን ይወጣል ሲሉም ገልጸዋል። የወላይታ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ወህዴግ) ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሚልክያስ ሳንታ በበኩላቸው መንግስት የባህር በር ለማግኘት የጀመረው ተግባር ወቅቱን የጠበቀ ትክክለኛ አካሄድ መሆኑን ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በታሪክም ይሁን በህግ ተገቢነት እንዳለው አንስተው ጉዳዩም የትውልዱ ጭምር መሆኑን አንስተዋል። መንግስት ለኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚያስፈልግ በይፋ መናገር ከጀመረ ወዲህ በዓለም አቀፍ ደረጃም አጀንዳ እየሆነ መምጣቱ ጥሩ ስኬት መሆኑን ጠቅሰው፣ ለስኬታማነቱም በተለይ የኢትዮጵያ አጎራባች ሀገራት ተባባሪ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል። የባህር በር መኖር ሀገሪቱ አሁን እያስመዘገበች ያለውን ፈጣን ዕድገት አጠናክሮ የማስቀጠል ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አቶ ሚልክያስ አንስተዋል። በመሆኑም ጥያቄው ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ በግልም ሆነ እንደ ፓርቲ ያላሰለሰ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ጊዜውን ጠብቆ የሚካሄድ ይሆናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 28, 2025 95
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ጊዜውን ጠብቆ የሚካሄድ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሔደ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ሲሆን በማብራሪያቸው፤ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ የተሻለ ይሆናል ብለዋል፡፡ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ጊዜውን ጠብቆ እንደሚካሄድ ገልጸው፤ ምርጫው አማራጭ ድምጾች ይበልጥ የሚካተቱበት እንደሚሆን ይጠበቃል ነው ያሉት። ለዚህም እንደ መንግስት እና ፓርቲ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠው፤ ይህን ለማስፈጸም በቂ አቅም እንዳለ ነው የተናገሩት፡፡ ምርጫውን ለማከናወን መንግስት በቂ አቅምና ዝግጁነት አለው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስካሁን በኢትዮጵያ ከተካሄዱ ምርጫዎች የተሻለ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም ብለዋል። ምርጫው ዴሞክራሲያዊና ብዘሃ ድምጾች ያሉት እንዲሆን በሃላፊነት እንሰራለን ሲሉም ገልጸዋል። እኛ እንደ ፓርቲም፤ እንደ መንግስትም ዝግጁ ነን ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከወዲሁ መዘጋጀት አለባቸው ነው ያሉት። በመሆኑም ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው ለመሳተፍ ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 28, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን እድገት የማይሹ ሀገራት በጦርነት እንደማያሸንፉን ያውቁታል ያላቸው ምርጫ ባንዳዎችን መላክ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያን በቅጡ ያላወቁ የውስጥ ባንዳዎች ደግሞ ከጠላት ጋር በማበር ዓላማቸውን የሚያሳኩ ይመስላቸዋል ይህ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት ችግሮች አሉኝ የሚሉ አካላት ጋር ቁጭ ብሎ በመነጋገር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አሁንም ክፍት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው ሲሉም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስገነዘቡት።
መንግሥት ወደ ሰላም ከሚመጣ  የትኛውም ኃይል ጋር አብሮ ለመስራት ሁልጊዜም ዝግጁ ነው 
Oct 28, 2025 66
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦መንግሥት ወደ ሰላም ከሚመጣ የትኛውም ኃይል ጋር ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን አብሮ ለመስራት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ የሚስተዋሉ የሰላምና የፀጥታ ችግሮች በዘላቂነት እንዲፈቱ መንግሥት ሰላምን ቀዳሚ አማራጭ አድርጎ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያን በሁለት እግር መቆም የማይፈልጉ ሀገራት በጦርነት ሊያሸንፉን እንደማይችሉ በደንብ ስለሚያውቁ ያላቸው አማራጭ ተላላኪ ባንዳዎችን መላክ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያን እገነጥላለሁ ወይም እጠቀልላለሁ የሚል ኃይል የኢትዮጵያን ባህል በቅጡ ባለማወቅ የፈጠረው ህልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጸረ ሰላም ኃይሎች ቀላል መንገድ የሚመስላቸው ከጠላት ጋር ማበር ነው ብለዋል። ይሄ ችግር ባለበት የተሟላ ሰላም ማምጣት የራሱ ችግር እንዳለበትም አስረድተው፥ ሰላም ትዕግስትና ጊዜ እንደሚፈልግ ጠቅሰዋል። ነፍጥ ካነሱ ወገኖች ጋር በመወያየት በሰላም ስልጣን የያዙና ከመንግሥት ጋር አብረው እየሰሩ የሚገኙ መኖራቸውን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገር ፍላጎት እስከ ተግባባን ድረስ የግል ጉዳይን መተው አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ መንግሥት በሰላማዊ መንገድ ከሚመጣ የትኛውም ኃይል ለመነጋገርና ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን አብሮ ለመሥራት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ታጣቂዎችን በመልሶ ማቋቋም ወደ ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ የማድረግ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። አሁንም ለሰላም በራችን ክፍት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ካልተደመርንና ካልተጋገዝን የኢትዮጵያን ችግሮች በአጠረ ጊዜ ልንፈታ እንደማንችል በመገንዘብ በሰላማዊ መንገድ አብሮ መስራት ይገባል ብለዋል።
ፖለቲካ
በየተቋማችን የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ እንተጋለን  - የመንግስት ሠራተኞች
Oct 28, 2025 51
ጎንደር/ ገንዳ ውሃ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡- በሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፏቸውን በማጎልበት በየተቋማቸው የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ በትጋት እንደሚሰሩ በጎንደር ከተማ የመንግስት ሠራተኞች ገለጹ። ሠራተኞቹ "የውጭ ባንዳዎችንና የውስጥ ባንዳዎችን ቅዠት በማምከን አንፀባራቂ ድሎችን እናስመዘግባለን " በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊ ሠራተኞቹ እንዳሉት፤ አገልግሎት አሠጣጥን በማዘመን ቀልጣፋና ፈጣን ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ይሰራሉ።   ከተሳታፊዎቹ መካከል አስካል ፀሐይ በሰጡት አስተያየት፤ የመንግስት ተቋማትን የአገልግሎት አሠጣጥ ለማዘመን የተጀመሩ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራሮች የተገልጋዩን እንግልትና ቅሬታ የሚፈታ መሆኑን አንስተዋል። ይህም የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ከመሰረቱ የሚፈታና ሠራተኛውም በተመደበበት መስክ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ምቹ የስራ ምህዳር የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ ሌላኛው ተሳታፊ መልካሙ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሠራተኛውን የስራ ተነሳሽነት የሚያጎለብትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እውቀቱንም ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት በተመረጡ ተቋማት የጀመራቸው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ ወደ ሁሉም ተቋማት እንዲሠፉ የሚደግፉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዲጂታል ቴክኖሎጂው የተገልጋዩን ጊዜ ፣ገንዘብንና ጉልበትን ቆጥቦ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ያሉት ደግሞ አቶ ባዘዘው ታምራት ናቸው፡፡ ሠራተኞቹ በሰላም ግንባታ ላይ ሲያደርጉ የቆዩትን ተሳትፎ በማጎልበት በየተቋማቸው የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ በታማኝነትና በቅንነት ተግተው እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሲርቪስና የሰው ሃብት ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ነጻነት መንግስቴ እንደገለጹት፤ መሶብ የአንድ ማዕከልን ጨምሮ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋና ፈጣን ማድረግ የሚያስችል ነው፡፡   በመንግስት ለሠራተኛው የተደረገው የደመወዝ ማሻሻያ የስራ ተነሳሽነቱን የሚያጎለብት በመሆኑ ሠራተኛው በሠላም ግንባታና በልማት እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክር አሳስበዋል፡፡ በተመሳሳይ የምዕራብ ጎንደር ዞን የመንግስት ሠራተኞች ውይይት አካሄደዋል።   በገንዳውሃ በተካሄደው ውይይት ከተሳተፉት ሠራተኞች መካከል ዮሐንስ ዓለሙ የውጭና የውስጥ ጠላቶችን ሴራ በአንድነት በማክሸፍ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ሌላው ተሳታፊ ግርማ ሰፊው ፤ ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባሻገር አፍራሽ አጀንዳዎችን ቀድሞ በመገንዘብ ለመመከት ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ አቋም በመያዝ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ የተናገሩት ደግሞ አትጠገብ አሻግሬ ናቸው።   የዞኑ ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ቢተው አሳየ በበኩላቸው፤ ነጠላ ትርክትን በማስወገድ ሀገሪቱ የያዘችውን የእድገት ጎዳና ማስቀጠልና ሰላምን ማፅናት ከሁሉም የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን አብራርተዋል። የመንግሥት ሠራተኛው ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት በመስጠት የሕብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ መትጋት እንዳለበት አሳስበዋል።
በሐረሪ ክልል የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ይጠናከራሉ
Oct 28, 2025 75
ሐረር ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በትኩረት ሊከናወኑ በሚገባቸው ተግባራት ዙሪያ ለክልሉ አመራር አባላት አቅጣጫ ሰጥተዋል። በወቅቱም ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ የሰላምና ልማት ስራዎችን የማረጋገጥ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።   ህገወጥ የመሬት ወረራና የቤት ግንባታ እንዲሁም ህገ ወጥ ንግድን የመከላከሉና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ተግባር በአመራሩ በትኩረት ሊከናወኑ ከሚገባቸው ተግባራት መካከል እንደሆኑም ጠቅሰዋል። በክልሉ በአሁኑ ወቅት የተጀመሩና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ሰፋፊ የልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት የማብቃት ስራ ላይ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። እንዲሁም በኮሪደር ልማት የተጀመሩ ስራዎች በተያዘላቸው ጊዜ ገደብ የማጠናቀቅ ስራን ማከናወን ይገባል ሲሉም አክለዋል። በበጀት ዓመቱ አዲስ በዕቅድ የተያዙ የወንዝ ዳርቻ ልማትና ሌሎች ስራዎችን በፍጥነት ወደ ስራ የማስገባት ተግባር ይከናወናል ብለዋል።   ከዚህም በተጨማሪ የገጠሩን ማህበረሰብ ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ በምርት አሰባሰብ ወቅት የምርት ብክነት እንዳይከሰት በማድረግ አርሶ አደሩ ምርቱን ለገበያ እስኪያቀርብ ድረስ ክትትል እና ድጋፍ ይደረጋል ሲሉም አክለዋል። በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ የመሰብሰብ ስራን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ተናግረዋል። ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ለማህበረሰቡ የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ስራን ማሳለጥ እንደሚገባም አመልክተዋል።  
የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው 
Oct 28, 2025 103
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፣ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊ (ጂኦግራፊያዊ)፣ ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ እናምናለን ብለዋል። ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን ለማጣት 30 ዓመት በላይ የወሰደ ትግል እንደነበር ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አገሪቷ ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ 30 ዓመት አያስፈልጋትም ብለዋል። ይህን ጉዳይ ለመፍታት በተረጋጋ፣ በሰከነ እና በውይይት መሄድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ "ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅብንም" ሲሉ በአጽንኦት ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልወሰነው፣ ተወካዮች ያላዩትና ካቢኔም ያልወሰነው ውሳኔ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ትልቅ ጉዳይ ማን ወሰነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ህጋዊ እና ተቋማዊ መሠረት የሌለው ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን በተከተለ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችውን ጥረት እንደግፋለን-የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Oct 28, 2025 110
ወላይታ ሶዶ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን ተከትላ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ በቁርጠኝነት እንደሚደግፉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ኢትዮጵያ ለዘመናት ስትጠቀመው የቆየው የባህር በር በታሪክ አጋጣሚ ከእጇ ወጥቶ ከወደብ አልባ ሀገራት ተርታ ተሰልፋ ቆይታለች። መንግስትም የኢትዮጵያዊያን የዘመናት ቁጭት ሆኖ የቆየውን የባህር በር ጥያቄ በይፋ በማንሳት በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል። ይህንንም የኢፌድሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮችና በፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ የመክፈቻ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር አጽንኦት መስጠታቸው የሚታወስ ነው። በጉዳዩ ላይ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢዜአ ያነጋገራቸው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት የባህር በር ጥያቄው የትውልዱ የዘመናት ቁጭትን የሚመልስ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ መንግስት የጀመረው ጥረት እንዲሳካ በቁርጠኝነት እንደሚደግፉ ተናግረዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ጎበዜ አበራ የባህር በር ለሀገር ሁለንተናዊ ልማትና ዕድገት መሰረት መሆኑን አንስተዋል።   ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ህግን በተከተለና ዲፕሎማሲየዊ በሆነ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት እንዲሳካም ምክር ቤቱ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። "ኢትዮጵያ ለዘመናት ስትጠቀምበት የነበረውን የባህር በር ማጣቷ ለድህነታችን አንድ ምክንያት ከመሆኑ በላይ የሚያስቆጭ ነው" ያሉት ደግሞ የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ አቶ ተፈራ ጎበና ናቸው።   የባህር በር ጥያቄን ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶችን ማጠናከር ለድርድር መቅረብ የለበትም ያሉት አቶ ተፈራ የጉዳዩ መሳካት ልማትና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ለማፋጠን አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። የባህር በር ለማግኘት መንግስት የጀመረው ተግባር ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ እውን እንዲሆን ፓርቲያቸው የሚጠበቅበትን ይወጣል ሲሉም ገልጸዋል። የወላይታ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ወህዴግ) ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሚልክያስ ሳንታ በበኩላቸው መንግስት የባህር በር ለማግኘት የጀመረው ተግባር ወቅቱን የጠበቀ ትክክለኛ አካሄድ መሆኑን ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በታሪክም ይሁን በህግ ተገቢነት እንዳለው አንስተው ጉዳዩም የትውልዱ ጭምር መሆኑን አንስተዋል። መንግስት ለኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚያስፈልግ በይፋ መናገር ከጀመረ ወዲህ በዓለም አቀፍ ደረጃም አጀንዳ እየሆነ መምጣቱ ጥሩ ስኬት መሆኑን ጠቅሰው፣ ለስኬታማነቱም በተለይ የኢትዮጵያ አጎራባች ሀገራት ተባባሪ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል። የባህር በር መኖር ሀገሪቱ አሁን እያስመዘገበች ያለውን ፈጣን ዕድገት አጠናክሮ የማስቀጠል ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አቶ ሚልክያስ አንስተዋል። በመሆኑም ጥያቄው ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ በግልም ሆነ እንደ ፓርቲ ያላሰለሰ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ጊዜውን ጠብቆ የሚካሄድ ይሆናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 28, 2025 95
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ጊዜውን ጠብቆ የሚካሄድ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሔደ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ሲሆን በማብራሪያቸው፤ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ የተሻለ ይሆናል ብለዋል፡፡ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ጊዜውን ጠብቆ እንደሚካሄድ ገልጸው፤ ምርጫው አማራጭ ድምጾች ይበልጥ የሚካተቱበት እንደሚሆን ይጠበቃል ነው ያሉት። ለዚህም እንደ መንግስት እና ፓርቲ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠው፤ ይህን ለማስፈጸም በቂ አቅም እንዳለ ነው የተናገሩት፡፡ ምርጫውን ለማከናወን መንግስት በቂ አቅምና ዝግጁነት አለው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስካሁን በኢትዮጵያ ከተካሄዱ ምርጫዎች የተሻለ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም ብለዋል። ምርጫው ዴሞክራሲያዊና ብዘሃ ድምጾች ያሉት እንዲሆን በሃላፊነት እንሰራለን ሲሉም ገልጸዋል። እኛ እንደ ፓርቲም፤ እንደ መንግስትም ዝግጁ ነን ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከወዲሁ መዘጋጀት አለባቸው ነው ያሉት። በመሆኑም ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው ለመሳተፍ ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 28, 2025 75
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን እድገት የማይሹ ሀገራት በጦርነት እንደማያሸንፉን ያውቁታል ያላቸው ምርጫ ባንዳዎችን መላክ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያን በቅጡ ያላወቁ የውስጥ ባንዳዎች ደግሞ ከጠላት ጋር በማበር ዓላማቸውን የሚያሳኩ ይመስላቸዋል ይህ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት ችግሮች አሉኝ የሚሉ አካላት ጋር ቁጭ ብሎ በመነጋገር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አሁንም ክፍት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ብቸኛው መንገድ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ነው ሲሉም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስገነዘቡት።
መንግሥት ወደ ሰላም ከሚመጣ  የትኛውም ኃይል ጋር አብሮ ለመስራት ሁልጊዜም ዝግጁ ነው 
Oct 28, 2025 66
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦መንግሥት ወደ ሰላም ከሚመጣ የትኛውም ኃይል ጋር ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን አብሮ ለመስራት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምና ጸጥታን በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ የሚስተዋሉ የሰላምና የፀጥታ ችግሮች በዘላቂነት እንዲፈቱ መንግሥት ሰላምን ቀዳሚ አማራጭ አድርጎ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያን በሁለት እግር መቆም የማይፈልጉ ሀገራት በጦርነት ሊያሸንፉን እንደማይችሉ በደንብ ስለሚያውቁ ያላቸው አማራጭ ተላላኪ ባንዳዎችን መላክ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያን እገነጥላለሁ ወይም እጠቀልላለሁ የሚል ኃይል የኢትዮጵያን ባህል በቅጡ ባለማወቅ የፈጠረው ህልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጸረ ሰላም ኃይሎች ቀላል መንገድ የሚመስላቸው ከጠላት ጋር ማበር ነው ብለዋል። ይሄ ችግር ባለበት የተሟላ ሰላም ማምጣት የራሱ ችግር እንዳለበትም አስረድተው፥ ሰላም ትዕግስትና ጊዜ እንደሚፈልግ ጠቅሰዋል። ነፍጥ ካነሱ ወገኖች ጋር በመወያየት በሰላም ስልጣን የያዙና ከመንግሥት ጋር አብረው እየሰሩ የሚገኙ መኖራቸውን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገር ፍላጎት እስከ ተግባባን ድረስ የግል ጉዳይን መተው አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ መንግሥት በሰላማዊ መንገድ ከሚመጣ የትኛውም ኃይል ለመነጋገርና ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን አብሮ ለመሥራት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ታጣቂዎችን በመልሶ ማቋቋም ወደ ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ የማድረግ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። አሁንም ለሰላም በራችን ክፍት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ካልተደመርንና ካልተጋገዝን የኢትዮጵያን ችግሮች በአጠረ ጊዜ ልንፈታ እንደማንችል በመገንዘብ በሰላማዊ መንገድ አብሮ መስራት ይገባል ብለዋል።
ማህበራዊ
የተመዘገበው ውጤት ለዘርፉ ትኩረት ከተሰጠ የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካት እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ ነው
Oct 28, 2025 29
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦በአገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው ውጤት ለዘርፉ ትኩረት ከተሰጠ የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካት እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ በ2017 ዓ.ም አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት ተሰጠ። ሽልማቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለተማሪዎቹ አስረክበዋል።   ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማዋ ከፍተኛ ውጤት ከተመዘገበባቸው ዘርፎች መካከል ትምህርት አንዱ ነው። መንግስት የትምህርት ስብራትን ለመጠገን አዲስ ፖሊሲና ሥርዓተ ትምህርት በመቅረጽ ተግባራዊ ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። የመማር ማስተማር ሥርዓቱን ምቹ የማድረግና የትምህርት ግብዓቶችን የማሟላት ሥራ በስፋት ሲሠራ መቆየቱን ገልጸው፤ በዚህም የተማሪዎች ውጤት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እና እያደገ መምጣቱን አመልክተዋል። በአገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው ውጤት ለዘርፉ ትኩረት ከተሰጠ የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካት እንደሚቻል ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።   በቀጣይ የመጣውን ውጤት እያበረታታን ለሌላ ስኬት ጠንክረን የምንሠራ ይሆናል ነው ያሉት። ተማሪዎች ዛሬ የተሰጣቸው ሽልማት በቀጣይ ሕይወታቸው ጠንክረው በመስራት ለአገራቸው የበኩላቸውን የላቀ ድርሻ እንዲያበረክቱ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።   ዛሬ በተሰጠው እውቅና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው ታብሌት ኮምፒውተር ተበርክቶላቸዋል። እንዲሁም ለመጣው ውጤት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና የትምህርት ማኅበረሰብ እውቅና ተሰጥቷል።
በተደረገልን አቀባበል ተደስተናል-አዲስ ገቢ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች
Oct 28, 2025 86
ሮቤ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡- በዩኒቨርሲቲው እና በአካባቢው ማህበረሰብ የተደረገልን አቀባበል በትምህርታችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መነሳሳትን ፈጥሮልናል ሲሉ በመደወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ተናገሩ። ዩኒቨርሲቲው 2 ሺህ 592 አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል።   አዲስ ገቢ ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲውና በአካባቢው ማህበረሰብ የተደረገላቸው አቀባበል በትምህርታቸው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መነሳሳትን እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል። አቀባበል ከተደረገላቸው አዲስ ገቢ ተማሪዎች መካከል ከሰሜን ሸዋ ዞን የመጣችው ቤተልሄም ቦጋለ በሰጠችው አስተያየት በዩኒቨርሲቲው የተደረገላቸው አቀባበል ልዩ ስሜት እንደፈጠረባት ተናግራለች።   በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋም ትኩረቷን በትምህርት ላይ በማድረግ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንደምትተጋ ገልጻለች። የተደረገላቸው አቀባበል በትምህርት ቆይታቸው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መነሳሳትን እንደሚፈጥር የገለጸው ደግሞ ከምዕራብ አርሲ ዞን የመጣው ተማሪ ሙዘይን አቡ ነው።   የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት ተማሪ ረመዳን ሉቅማን በበኩሉ የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት አባላትና በጎ ፈቃደኛ ነባር ተማሪዎች በማቀናጀት ለአንደኛ ዓመት ተማሪዎቹ አቀባበል እያደረጉ መሆኑን ተናግሯል።   የዩኒቨርሲቲው ዋና ሬጂስትራር ዳይሬክተር አብዱልሀይ አብደላ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው የተመደቡለትን 2 ሺህ 592 የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው።   ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎቹን ተቀብሎ የመማር ማስተማር ሥራውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የመኝታ፣ የመማሪያና የመመገቢያ ክፍሎች እንዲሁም የመማርያ ቁሳቁስ ዝግጅት ማድረጉን አመልክተዋል። አዲስ የተቀበላቸውን ጨምሮ ከ20 ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎችን በተለያዩ መርሃ ግብሮች እያስተማረ መሆኑም ተመልክቷል። በቅበላ መርሐ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችን ጨምሮ የተማሪዎች ህብረት አባላት፣ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
በኢትዮጵያ 63 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች የጤና መድህን ተጠቃሚ ሆነዋል
Oct 28, 2025 81
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ 63 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች በጤና መድህን ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ውስጥ የጤና መሰረተ ልማቶችን ለማስፋት እየተሰራ ነው። በኢትዮጵያ 63 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች በጤና መድህን ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህም በርካታ ዜጎች የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረጉን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል። የመድሃኒት አቅርቦትን በተመለከተ ከውጭ የሚገቡ መድሃኒቶች ለመቀነስና በአገር ምርቶች ለመተካት ሙከራ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የጤናውን ዘርፍ ለማስፋትና የህዝቦችን የጤና አገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። ለአብነትም የቅዱስ ጵውሎስ ሆስፒታል አንድ ሺህ አልጋ ያለው የመሰረተ ልማት ግንባታ ማደረጉን ገልጸው፤በቀጣይ አስፈላጊው ግብዓት ተሟልቶ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረግ ገልጸዋል።
የትምህርት ጥራትን የሚያሻሽሉና ትውልድን የሚገነቡ ስራዎች በስፋት እየተሰሩ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 28, 2025 73
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን የሚያሻሽሉና ትውልድን የሚገነቡ ስራዎች በስፋት እየተሰሩ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ በተካሄደው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው እንድገለጹት፤ የትምህርቱን ጥራት ለማስጠበቅ ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ ትውልድን የሚገነቡና የሚያንጹ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው። ከእነዚህ መካከልም በትምህርት ተቋማት አካባቢ የሚገኙ አዋኪ ድርጊቶችን የማጥራት እንዲሁም በትምህርት ለትውልድ ፕሮጀክት የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ለመምህራን የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ከመስጠት ባሻገር በትምህርትና በፈተና አሰጣጥ ላይ ለውጥ እንዲመጣ መደረጉን ገልጸዋል። በትምህርት ቤት አካባቢዎችም የስፖርት ማዘውተሪያና የመዝናኛ ስፍራዎችን በመገንባት ጤናማ ትውልድ መገንባት መጀመሩን ነው የተናገሩት። በዘንድሮው የትምህርት ዘመንም ከ43 ሚሊየን በላይ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የመማሪያ መጻሕፍት መታደሉንና ይህም የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ከተሰሩ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆኑን ገልፀዋል። የተማሪዎች ምገባን በተመለከተም አስደናቂና ማሕበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስራዎች በመስራት ሁሉም የሚመኛት ኢትዮጵያ እንድትሆን እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።
ኢኮኖሚ
አፍሪካ የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ለመሙላት በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር ፈሰስ ማድረግ አለባት - የአፍሪካ ህብረት
Oct 28, 2025 38
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፦ አፍሪካ የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ለመሙላት በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እንደሚገባት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ በአንጎላ ሉዋንዳ ተጀምሯል። በጉባኤው መክፈቻ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የአፍሪካ ሀገራትና መንግስታት መሪዎችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር አፍሪካ የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ለመሙላት በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እንደሚገባት ገልጸዋል። መሰረተ ልማት የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የጀርባ አጥንትና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ የመሰረተ ልማት ፕሮግራም(ፒዳ) በአህጉሪቱ 16ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ እና አራት ሺህ ኪሎ ሜትር የባቡር መንገድ ግንባታ መከናወኑን ጠቁመው 30 ሚሊዮን ዜጎች ኢነርጂ ተደራሽ ማድረጉን አመልክተዋል። በሀገር በቀል የሀብት ማሰባሰብ፣ በአማራጭ ፋይናንስና በጠንካራ ዓለም አቀፍ አጋርነት አማካኝነት በቀጣይ ምዕራፍ የፕሮግራሙን ስኬታማነት የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰራ ተናግረዋል። የአፍሪካ የትስስር አጀንዳ ራዕይ ብቻ ሳይሆን የአህጉሪቱ ስኬቶች በተግባር የሚረጋገጥበት መንገድ ጭምርም ነው ብለዋል። የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ ጉባኤው በአፍሪካ የሚገነቡ ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክቶች ሀብት የማሳባሰብና አፈጻጸም ደረጃ የሚገመገምበት መሆኑን አመልክተዋል። ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ እስከ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚቆይ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጥራትና ጊዜ እንዲጠናቀቁ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል ይደረጋል
Oct 28, 2025 39
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያን ከበለጸጉ ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ መሰረት የሚጥሉ ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጥራትና የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን አጠናቃ ባስመረቀችበት ማግስት የጉባ ብስራቶች የሆኑ የ30 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ይፋ አድርጋለች፡፡ እነዚህ ፕሮጀክቶች የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ግንባታ፣ የኒውክሌር ሀይል ማበልጸጊያ፣ የጋዝ ማምረት፣ የነዳጅ ማጣሪያ እና በስድስት ዓመታት ውስጥ ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ ቤቶች ግንባታ ናቸው፡፡ ፕሮጀክቶቹ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠርና የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት ለሕዝቡ የመልማት ፍላጎት ምላሽ የሚሰጡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ሀገራዊ ፕሮጀክቶቹ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በመሰረታዊነት የሚቀይሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል መብራቱ መለስ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ ትላልቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡   ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶቹ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሽግግር የሚያፋጥኑ ወሳኝ ርምጃዎች መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡ ሌላው የምክር ቤት አባል አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) ፕሮጀክቶቹ ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ስሟ በድህነት ሲጠቀስ የነበረበትን የታሪክ ምዕራፍ የሚቋጩ እና በሌላ ገጽታ የሚያስተዋውቁ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡   ግንባታቸው የተጀመሩና በሂደት ላይ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያን ካደጉ ሀገራት ተርታ የሚያሰልፉ መሆናቸውን ገልጸው፤ የኢትዮጵያን በጎ ገጽታም ይገነባሉ ብለዋል፡፡ ሌላዋ የምክር ቤት አባል አዲሷ አሰፋ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለአፍሪካ ትሩፋት የሚሆኑ የልማት ፕሮጀክቶችን እውን ማድረጓን ገልጸዋል፡፡   ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉም አረጋግጠዋል፡፡ የምክር ቤት አባላቱ ምክር ቤቱ በህገ መንግስቱ በተሰጠው ስልጣን መሰረት የፕሮጀክቶችን ገቢራዊነት ይከታተላል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ  የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ የበኩላችንን እየተወጣን ነው - የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት
Oct 28, 2025 52
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በሰላማዊ፣ በሰጥቶ መቀበልና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል።   በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያን ቀይ ባህርን እንድታጣ ያደረገውን ውሳኔ ማን ወሰነ ብለን ስንፈልግ ተቋማት አልገቡበትም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም ብለዋል።   ኢዜአ ያነጋገራቸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፍትሃዊ፣ ምክንያታዊና የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክር ቤት አባል አቶ ሳዲቅ አደም እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዓለም አቀፍ የሕግ ማዕቀፍና በተለያዩ ኮንቬንሽኖች ተቀባይነት ያለው ነው ።   ኢትዮጵያ ከባህር በር ርቃ የቆየችበት መንገድ ተገቢ አለመሆኑን ጠቁመው፤ የኢትዮጵያ ጥያቄ የሰጥቶ መቀበል መርህን እና ሰላማዊ መንገድን ያስቀደመ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ስኬታማ እንዲሆን ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ አሳስበው፤ ምክር ቤቱም አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ ላይ መሆኑን ተናግረዋል። የምክር ቤት አባል አስቴር ከፍታው በበኩላቸው፤ የባህር በር ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል፡፡   ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚ መሆን የምትፈልገው በሰላማዊ መንገድ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህ ስኬት የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ መላው ሕዝብ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በፍጥነት እያደገ በመምጣቱ የባህር በር ይህንኑ ፍላጎት ለማሳካት መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤት አባል አምባሳደር ተውፊቅ አብዱላሂ (ዲ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የመላው ሕዝብ አጀንዳ መሆኑን ተናግረው፣ አጀንዳው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ገልጸዋል።   የኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚነት ጥያቄ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተመሰረት መሆኑን ጠቁመው፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት አለበት ብለዋል። ፍትሐዊ የሆነው ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ አስፈላጊውን ሁሉ በማድረግ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከአማራ ክልል በያዝነው ዓመት 170 ሺህ ኩንታል ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለገበያ ለማቅረብ ታቅዷል
Oct 28, 2025 48
‎ባህርዳር ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ከአማራ ክልል በያዝነው ዓመት 170 ሺህ ኩንታል ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ‎በቢሮው የሆልቲካልቸር ባለሙያ አቶ አወቀ ዘላለም ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ የቡና ልማትን በማስፋፋትና ምርታማነቱን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። ‎‎በክልሉ በስነ ምህዳርና በአየር ንብረታቸው ተስማሚ በሆኑ አካባቢዎች በኩታ ገጠም ጭምር ከ34 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የቡና ልማት እየተካሄደ መሆኑን ገልፀዋል። ‎ከዚህ ውስጥም ምርት መስጠት ከጀመረው 25 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ 170 ሺህ ኩንታል ጥራቱን የጠበቀ ቡና በማምረት ለአካባቢና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የለቀማና ምርት ስብስባ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።   ‎አሁን ላይ ‎‎ለአምራች አርሶ አደሮች ስለቡና ምርት አሰባሰብ፣ አደራረቅና አዘገጃጀት ግንዛቤ በመፍጠር ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለማቅረብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ‎‎በምዕራብ ጎጃም ዞን የጃቢጠህናን ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ውበት ተስፌ ግማሽ ሄክታር በሚጠጋ መሬታቸው ላይ የተሻሻለ ምርት የሚሰጥ የቡና ዝርያ እያለሙ መሆኑን ተናግረዋል። ‎ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለገበያ ለማቅረብ ‎የደረሰውን ምርት እየለቀሙ በአልጋ ላይ በማድረቅ እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል። ‎‎የተሻሻለ የቡና ዝርያ በሩብ ሄክታር መሬታቸው ላይ በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የዳንግላ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙላቱ እንግዳ ናቸው።   ‎‎ዘንድሮ ወቅቱ ለቡና ልማት ተስማሚ በመሆኑ የተሻለ የቡና ምርት በመሰብሰብና በመሸጥ ከሰብል ልማቱ ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። ‎በክልሉ ባለፈው በጀት ዓመት 130 ሺህ ኩንታል ቡና ለገበያ መቅረቡን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ያሳድጋል 
Oct 28, 2025 40
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት የሕክምና አገልግሎትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ፋይዳው የጎላ መሆኑን በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። በቅርቡ ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕላንት ፕሮጀክት ከሀይል አማራጭነት የዘለለ የተለያዩ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ከእነዚህ ጠቀሜታዎች መካከል አንዱ የኒኩሌር ህክምና አገልግሎት ይገኝበታል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መምህር፣ ሀኪም፣ ተመራማሪና የካንሰር ሕክምና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን ሁነኛው ለኢዜአ እንደገለፁት የኒኩሌር ፕላንቱ በሕክምናው ዘርፍ ለኢትዮጵያ ትልቅ እድል ይዞ የሚመጣ ነው። በተለይ በዋናነት የካንሰር በሽታን ለማከም ያለው ፋይዳ ላቅ ያለ በመሆኑ የህክምና አገልግሎቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደርሰዋል ብለዋል። አክለውም ለራዲዮ ቴራፒ ሕክምና የሚውሉ መድሀኒቶችን ለማምረትና የቆይታ ጊዜያቸው ከስምንት ቀን የማይበልጡ መድሀኒቶችን ብልሽት መፍታት ያስችላል ነው ያሉት። ከኒኩሌር ጋር በተያያዘ መንግስት የወሰደው ኢንሼቲቭ ከህክምና አገልግሎቱ ባለፈ በዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያለው ፋይዳም ከፍተኛ በመሆኑ መበረታታት እንዳለበት ዶክተር ሰለሞን ተናግረዋል።   ሌላው የዩኒቨርሲቲው መምህርና የህጻናት ካንሰር ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሙሉአለም ንጉሴ በበኩላቸው ያደጉ ሀገሮች የኒኩሌር ሕክምናን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠቀሙበት አንስተዋል። የኒኩሌር ሀይል ለአዋቂም ሆነ ለሕጻናት ሕክምና የበሽታውን ሁኔታና ያለበትን ደረጃ ለይቶ ለማከም ያለው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ፕሮጀክቱ ለሕክምናው ዘርፍ ጭምር ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ብለዋል። የኒኩሌር ሀይል ለካንሰር ሕክምና አገልግሎት ሦስት ዋና ዋና ፋይዳ አለው ያሉት ባለሙያው የካንሰር አይነቱንና የስርጭቱን መጠን እንዲያውቅ ይረዳዋል ነው ያሉት። ሕመምተኛውም የበሽታው አይነትና ስርጭትን መሰረት ያደረገ ሕክምና እንዲያገኝ እንደሚያስችለው ገልጸዋል። ለካንሰር ሕሙማን የኒኩሌር ሕክምና በሀገር ውስጥ ስለማይሰጥ ሕክምናውን ለማግኘት ወደ ውጪ እንደሚላኩ የገለጹት ዶክተር ሙሉአለም በዚህም ምክንያት ለወጪና እንግልት ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል።   የኒኩሌር ሕክምና ከሌሎቹ የሲቲ ስካን፣ ኤም አር አይ እና ሌሎች መሳሪያዎች አንጻር ያለውን በሽታ ለይቶ ማሳየት ብቻ ሳይሆን ያደረሰውን የጉዳት መጠን ጭምር ለይቶ የሚያሳይ ነው ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የሕክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ክብሩ ክፍሌ ናቸው። በካንሰር የተጠቃ የሰውነት አካል ምን ያህል እንደተጎዳ፣ የትኛው ክፍሉ ሥራውን በአግባቡ እያከናወነ እንደሚገኝ የሚለውን በትክክል መለየት የሚያስችል የዘመናዊ ሕክምና ትልቅ መሳሪያ መሆኑን አስረድተዋል። እንደ ሀገር ይፋ የተደረገው የኒኩሌር ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ከፍ ወዳለ ደረጃ የሚያሸጋግር በመሆኑ መንግስት የወሰደው ተነሳሽነት ሊበረታታና ሊደገፍ ይገባል ሲሉም ምሁራኑ ገልፀዋል።
በዲጂታል ዘርፉ ላይ የተደረገው ሪፎርም በዘርፉ ከፍተኛ  እድገት እንዲመዘገብ አድርጓል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 
Oct 28, 2025 67
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦በዲጂታል ዘርፉ ላይ የተደረገው ሪፎርም በዘርፉ ከፍተኛ እድገት እንዲመዘገብ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሄዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የ2025 የዲጂታል ቴክኖሎጂ አካታች የ2030 ስትራቴጂ በመጀመር በዘርፉ የተሻለ እድገት ለማስመዝገብ እየሰራች ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ኮደርስ ስልጠና 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች ስልጠናውን በነጻ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ለውጡ በተጀመረበት ወቅት 37 ሚሊዮን የቴሌኮም ተጠቃሚዎች እንደነበሩ ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት ቁጥሩ 93 ሚሊዮን ደርሷል ነው ያሉት። ይህም ሪፎርም በዘርፉ ትልቅ እድገትና ለውጥ እንዲመዘገብ ማድረጉን አመላካች ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት 55 ሚሊዮን የሚደርሱ ዜጎች ዲጂታል ባንኪንግ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በ2028 ዘርፉ 11 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ሃብት ያመጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል። ከዚሁ ዘርፍ 1 ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጠር የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህም 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደሚገኝ መተንበዩንም ነው የተናገሩት፡፡ በተለይ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍም ሰፋፊ ለውጥና ብቃት እየተመዘገበ መሆኑን አብራርተው፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጨምሮ ከሚጠበቀው በላይ ስኬታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዲጂታል ዘርፉ ላይ የተካሔደው ሪፎርም ኢትዮጵያ በራሷ አቅም የዲጂታል ገበያ ላይም ስኬታማ ስራዎች እየሰራች መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና ወስደዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Oct 28, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ወቅት ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታላይዜሽንን በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና ወስደዋል ብለዋል። ይህ ትልቅ ቁጥር መሆኑን ጠቁመው 93 ሚሊዮን ደንበኞች ደግሞ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ሲሆኑ 55 ሚሊዮን ዜጎች የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ሲሉም ገልጸዋል። ይህ ኢትዮጵያን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የጀመረነው ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን አመላካች ነው ሲሉክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል።
ስፖርት
የአርባ ምንጭ ስታዲየም ግንባታን አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ጥረት እየተደረገ ነው
Oct 28, 2025 54
አርባምንጭ ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ) :- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የአርባ ምንጭ ስታዲየም ግንባታን በሕብረተሰቡ ተሳትፎ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ። ለስታዲየሙ ግንባታ ድጋፍ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ዛሬ በአርባምንጭ ከተማ ተካሄዷል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ እየተገነባ ያለው የአርባምንጭ ስታዲየም ለዞኑ፣ ለክልሉ ብሎም ለሀገሪቱ እግር ኳስ ዕድገት የበኩሉን አሰተዋጽኦ ይኖረዋል። በአካባቢው ለእግር ኳስ ተሰጥኦ ያላቸው ስፖርተኞች እንዳሉ አውስተዋል። ስታዲየሙ ግንባታው 30 በመቶ መድረሱን ጠቁመው ለሀገር ተተኪና ተወዳዳሪ ስፖርተኞች ለማፍራት የሚደረጉ ጥረቶች ዕውን እንዲሆን ያግዛል ብለዋል። የስታዲየሙን ግንባታ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ሕዝቡን የሚያሳትፍ የተለያዩ የገቢ ማስገኛ ዘዴዎች መመቻቸታቸውን አስረድተዋል። ከእነዚህ መካከልም በቴሌ አጭር መልዕክትና ቶምቦላ ሎተሪ ይጠቀሳሉ ብለዋል። በትልቅ አስበን በትልቅ ጀምረናል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ ለጋራ የሆነው ፕሮጀክት በተባለለት ጊዜ እንዲጠናቀቁ በየደረጃው የሚገኘው ሕብረተሰብ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል መልዕከት አስተላልፈዋል።   የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአርባምንጭ ስታዲየም በሕዝብና በመንግስት ትብብር የሚገነባ መሆኑን ገልጸዋል። የ33 ወራት ውል ተገብቶ እየተከናወነ የሚገኘው የስታዲየሙ ግንባታ በአንድ ዓመት ቆይታ ሂደት 30 በመቶ ደረጃ መድረሱን አስታውቀዋል። የስታዲየሙ ግንባታ ከአካባቢው አልፎ የሀገር ፕሮጀክት በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተለያየ መንገድ ድጋፋቸውን እየገለጹ መሆኑን አንስተዋል። በቻይና ኮሙኒኬሽን እና ኮንስትራክሽን ካምፓኒ (ሲሲሲሲ) ተቋራጭነት እየተገነባ ያለው የአርባ ምንጭ ስታዲየም 25 ሺህ ሰዎችን የሚይዝና የመሮጫ ትራክን ጨምሮ ሌሎች ስፖርቶችን ማስተናገድ የሚችል ስፍራ እንደሚኖረው ተመላክቷል።  
አካባቢ ጥበቃ
በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደናቂ የልማት ስኬት ማስመዝገብ ተችሏል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Oct 28, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡-በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደናቂ የልማት ስኬት ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው። በመደበኛ ስብሰባው ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምላሽና ማብራሪያቸው፤ 2017 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ የታሪክ እጥፋት ውስጥ ይቻላሉ ተብሎ የማይታሰቡ ጉዳዮች የተቻሉበት የስኬት ዓመት እንደነበር ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ያነገባቸውን ዓላማዎችና ያስገኛቸውን ውጤቶች አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአንድ ዘርፍ ላይ ተንተርሶ ከድህነት ሊወጣ አይችልም በሚል ብዝኅ ዘርፍና ብዝኃ ተዋናይ የኢኮኖሚ አቅጣጫ ላይ የተነደፈው ፖሊሲ በእጅጉ ውጤታማ እየሆነ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎች ሳይዘነጉ አምስቱ ግንባር ቀደም የተሰናሰሉ በብዝኅ ዘርፍ ቢመሩ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እንደሚያሻሽሉ እምነት መጣሉን አስረድተዋል። ግብርና እና ማዕድን ለኢንዱስትሪ ግብዓት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ ኢንዱስትሪውም ግብርናን የሚያፋጥን ማሽን ፈጣሪ ነው ብለዋል። ቴክኖሎጂ የታከለበት ብዝኅ ዘርፍ የኢኮኖሚ ልማትም ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ያስቻለ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ እንደሚገኝ አንስተዋል። የብዝኅ ተዋናይነትም መንግስት አንድ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ በመሆን ከግሉ ዘርፍ፣ ከህዝብና የልማት አጋሮች ጋር ተሳስሮ የኢትዮጵያን ልማት በየፈርጁ ማፋጠን አለበት የሚል እምነት መያዙን ገልጸዋል። የግልና መንግስት አጋርነት እሳቤ ያለ ቢሆንም የመንግስትና ህዝብ አጋርነት ግን ግልጽ አቅጣጫ የተቀመጠለት ከለውጡ በኋላ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም በመንግስት የህዝብ አጋርነት ኢትዮጵያ በርካታ ስኬቶች ማስመዝገቧን ጠቅሰው፤ ለዚህም የአረንጓዴ አሻራ 48 ቢሊየን ችግኞች ስኬት ማሳያ ነው ብለዋል። እያንዳንዱ ችግኝ ከጅምሩ እስከ ተከላ መርሃ ግብሩ ባለው ሂደት አንድ ዶላር ቢወስድ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ 48 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስት ማድረግ መቻሏን አስረድተዋል። በዚህም ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ያለመታከት ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን በመስጠት በየዓመቱ ስለሰሩ ይህን ያክል ሃብት ያስወጣ የነበረን ስራ በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር ማሳካት ተችሏል ብለዋል። በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ የሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለቀጣናው ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ልማት እንዲሁም ለጋራ ብልፅግና መሪ ሚና እየተወጣች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Oct 27, 2025 152
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 17/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለቀጣናው ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ልማት እንዲሁም ለጋራ ብልፅግና መሪ ሚና እየተወጣች ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 2ኛውን የኢትዮጵያ የውሃ እና ኢነርጂ ሳምንት በሳይንስ ሙዚየም አስጀምረዋል።   በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል፣ ለውሃ እና ለአረንጓዴ ልማት በሰጠችው ትኩረት ለውጥ እያመጣች ሚሊዮኖችን ተጠቃሚ እያደረገች መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የቀጣናው የኃይል ማዕከል እየሆነች ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለጂቡቲ፣ ለሱዳንና ለኬንያ ታዳሽ ኃይል እያቀረበች ነው ብለዋል። በቅርቡም ወደ ሌሎች ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እንደምትልክ ጠቅሰው፥ ይህም የጋራ ቀጣናዊ የብልጽግና ራዕይዋ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዚህ የላቀ ራዕይ ምሰሶ እንደሆነ ገልጸው፥ ግድቡ ጽናታችንን፣ አንድነታችንንና በአፍሪካ መጻኢ የጋራ ህልሞች ላይ ያለንን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል። የግድቡ አገልግሎት ከኃይል ልማት ባሻገር ለብዝኃ ህይወት ጥበቃ፣ ጎርፍን ለመከላከልና በታችኛው ተፋሰስ ላሉ ሀገራት የተስተካከለ የውሃ ፍሰት እንዲያገኙ ያስችላል ነው ያሉት። ከፉክክር ይልቅ የጋራ ተጠቃሚነትንና ትብብርን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን በማንሳትም፥ ኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞቿ የቀጣናው የትስስር መሠረቶች ናቸው በሚል ግልፅ አቋም እየሠራች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ለአብነትም በአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ ግብር ባለፉት ዓመታት ከተተከሉ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች አንድ ሦስተኛ ያህሉ በዓባይ ተፋሰስ መተከላቸውንና ይህም ለሌሎች ሀገራት ፋይዳው የላቀ መሆኑን አስረድተዋል።   በሌላ በኩል ኢኮኖሚያችን እያደገ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የባህር በር ማግኘት ለቀጣይ እጣፈንታችን ዋስትና የሚሰጥ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የባህር በር ለኢትዮጵያ የግድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የባህር በር ማግኘት ንግድን ለማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ውህደትን ለማጎልበትና ቀጣናዊ ትብብርን ለማሳደግ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር እጣፈንታዋ የተሳሰረ በመሆኑ በጋራ ለመልማት እና ዘላቂ ጥቅምን ለማስጠበቅ በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት እየሠራች ነው ብለዋል። አፍሪካ ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ዋስትናዋን እንድታረጋግጥ ኢትዮጵያ መሪ ሚናዋን መወጣቷን እንደምትቀጥልም አረጋግጠዋል።
‎እምቦጭን በዘላቂነት ለመከላከል የህብረተሰብ ተኮር ሥራ ውጤት እያስገኘ ነው
Oct 26, 2025 185
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ)፡-እምቦጭን በዘላቂነት ለመከላከል የህብረተሰብ ተኮር ሥራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ‎በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ ሞቱማ መቃሳ ገለጹ፡፡ በውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ ሞቱማ መቃሳ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ያቀደቻቸውን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች ለማከናወን የውኃ ሀብቷን መጠበቅ ወሳኝ ነው። ስለሆነም መንግስት በአገሪቷ የልማት እቅዶች ውስጥ የውኃ አስተዳደርና ጥበቃን ቅድሚያ ሰጥቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ‎ለአብነትም በአገሪቷ ውስጥ ምን ያህል የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውኃ ሀብት እንዳለ በትክክል የመለየትና የመመዝገብ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   ‎ይህን ሀብት ለየትኞቹ የልማት ዘርፎች በምን ያህል መጠንና ጥራት ለማዋል እንደሚቻል የውኃ አቅም ልየታ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የውኃ ሀብት አስተዳደርና ጥበቃ ስራ ከፍ ብሎ እንዲመራ ሚኒስቴሩ መዋቅራዊ ማሻሻያ ማድረጉንም አመልክተዋል። ‎ከፍተኛ ትኩረት ከሚሹ የውኃ አካላት ጥበቃ ጉዳዮች መካከል አንዱ በእምቦጭ አረም ምክንያት የሚከሰተውን ችግር ማቃላል መሆኑን አመልክተዋል። ‎እምቦጭ በፍጥነት የሚስፋፋና በየጊዜው ተመልሶ የሚመጣ መሆኑን ያወሱት አቶ ሞቱማ፤ በዘላቂነት ለማቃለል በየጊዜው አስቸጋሪ ፈተና መሆኑን አንስተዋል። ይህንን ችግር መፍትሄ ለመስጠት ሚኒስቴሩ በትኩረት እየሰራበት እንደሚገኝም አብራርተዋል። ‎ይህን ዘላቂ ችግር ለማቃለል ህብረተሰብን ያማከለ አሰራር ተቀይሶ በመተግበር ላይ እንደሚገኝና ውጤትም እየተገኘበት እንደሆነም አስታውቀዋል። በጣና ሐይቅና በሌሎች የውኃ አካላት ላይ የእምቦጭ አረምን ችግር ለመፍታት ከተጀመሩ ሥራዎች በተጨማሪ ህብረተሰብ ተኮር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ሞቱማ ተናግረዋል። ‎የውኃ ሀብት ጥበቃና አስተዳደር የሀገር ጉዳይ በመሆኑ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና መላው ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የደን ሽፋን ማደግና የፓርኮች ልማት አዕዋፍትንና የዱር እንስሳትን ከስደት ታድጓል
Oct 26, 2025 146
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ)፡-በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተከናወነው ሥራ የደን ሽፋን ማደግና የፓርኮች ልማት አዕዋፍትንና የዱር እንስሳትን ከስደት እየታደገ መምጣቱን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ ገለጹ። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን 16ኛውን ዓለም አቀፍ የስደተኛ አዕዋፍ ቀንን "ለአዕዋፍት የተመቸ ማህበረሰብ እና ከተማ እንፍጠር" በሚል መሪ ሃሳብ በአቢጃታ ሻላ ሐይቆች ብሔራዊ ፓርክ አክብሯል።   የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ቀኑን ማክበር ያስፈለገው ለህብረተሰቡ ስለ እንስሳት ሀብት ጥበቃ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው። አዕዋፋትና የዱር እንስሳት በመኖሪያ አካባቢያቸው በሚደርስ መራቆት ምክንያት ለስደት እንደሚዳረጉ ተናግረው፤ በዚህም ኢትዮጵያ ከዘርፉ ማግኘት ያለባትን ጥቅም ሳታገኝ መቆየቷን ገልጸዋል።   የአዕዋፍት እና የዱር እንስሳት ስደት ችግርን ከስር መሰረቱ ለመፍታት የጥበቃ ቦታዎችን ማልማትና ማስፋፋት እንደሚገባ ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በተከታታይ በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአገር ደረጃ የደን ሽፋን ማደጉን ያወሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ይህም ለዱር እንስሳት ምግብና መጠለያ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው አብራርተዋል። የአካባቢ ጥበቃ እያደገ በመምጣቱ ሐይቆችም ወደ ድሮ ይዞታቸው መመለሳቸውን አመላክተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ባለፉት ጥቂት ዓመታት ፓርኮችን የመጠበቅ እና አዳዲስ የጥበቃ ስፍራዎችን የማልማት ተግባራት በስፋት ማከናወናቸውን ጠቁመዋል።   በአሁኑ ወቅት የአዕዋፋት እና የዱር እንስሳት ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን አመልክተው፤ የፓርኮችን ይዞታ በማሻሻልና ያሉትን በመጠበቅ ተሰደው የቆዩ የዱር እንስሳት ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው እንዲመለሱ ማስቻሉንም አስታውቀዋል። የዱር እንስሳት ለአደጋ ተጋላጭነት በእጅጉ እየቀነሰ መምጣቱን አንስተዋል። ኢዜአ ከነጋገራቸው ጎብኝዎች መካከል አቶ ዘሪሁን ግርማ ፤ መንግስት ከባለድርሻ አካላት ጋር በደን ልማትና በዱር እንስሳት ጥበቃ ላይ እያከናወነ ያለው ተግባር ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል፡፡   ሌላኛዋ ከቻይና የመጡት ጎብኝ ፒንግ ሁ በበኩላቸው፤ አቢጃታ ሻላ ሐይቆች ብሔራዊ ፓርክ ከዚህ በፊት አውቀዋለሁ፤ ሃይቆች ለመጥፋት የተቃረቡና ደኖችም ጥበቃ የማይደረግላቸው ነበሩ ብለዋል፡፡   አሁን ግን እጅግ ተለውጠው ሳቢ እና ማራኪ ሆነዋል፤ አዕዋፋትና የዱር እንስሳትንም በብዛት ተመልክቻለሁ ነው ያሉት፡፡ አቶ ጌትነት አማረ በበኩላቸው፤ መንግስት በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ላይ እያከናወነው ያለው ተግባርና እየመጣ ያለው ለውጥ የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡   በጉብኝቱ በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩማር፣ ባለድርሻ አካላት፣ አርቲስቶች፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና የባለስልጣኑ ሰራተኞች ተገኝተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው  
Oct 24, 2025 270
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡   በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡   ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡   በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀመረ
Oct 24, 2025 189
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦11ኛው የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተሞች በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው። በፎረሙ ላይ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች ምክክር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በቀጣናው መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከል የተጀመሩ የቅንጅት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኢጋድ
Oct 20, 2025 390
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 10/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ። የኢጋድ ሶስተኛው የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት የሚኒስትሮች ስብሰባ ዛሬ በኬንያ ናይሮቢ ተጀምሯል። “በኢጋድ ቀጣና ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሰራተኛ ፍልሰት እና የሰዎች ዝውውር ህጋዊ ማዕቀፍን ማሻሻል” የስብሰባው መሪ ቃል ነው። በስብሰባው ላይ የኢጋድ አባል ሀገራት የሰራተኛ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች፣ ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(አይኤልኦ)፣ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት(አይኦኤም)፣ የአውሮፓ ህብረትና የልማት አጋሮች ተገኝተዋል። በኢጋድ ቀጣና የሰራተኛ፣ ስራ እና የሰራተኛ ፍልሰት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በቀይ ባህር መስመር ያለውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ከኢጋድ ቀጣና ውጪ የሚገኙ ዜጎች አባል ሀገራትን በነጠላ የመግቢያ ቪዛ መጎብኘት የሚያስችላቸውን የቪዛ ኢኒሼቲቭ ይፋ ይደረጋል። ኢኒሼቲቩ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርና ድንበር ተሻጋሪ ንግድን ማሳለጥ እንዲሁም ቱሪዝምን የማሳደግ ፋይዳ እንዳለው ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአውሮፓ ህብረት የፋይናንስ ድጋፍ የሚተገበረው ነጻ የሰዎችና የቁም እንስሳት እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፍ ሁለተኛ ምዕራፍ ይፋ ይሆናል። ማዕቀፉ ህጋዊ የፍልሰት መንገዶች ለማጠናከር እና ቀጣናዊ ትስስርን የማሳካት ግብ ያለው መሆኑንም አመልክቷል። ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ሰንሰለትን መበጣጠስ፣ በፍልሰት በሌላ ሀገር የሚገኙ ዜጎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ላይ ምክክር ያደርጋሉ። በውይይቱ ማብቂያ ሀገራት የጋራ መግለጫ እንደሚያወጡ የሚጠበቅ ሲሆን ደህንነቱ የተጠበቀ መደበኛ ፍልሰት፣ ጠንካራ የሰራተኛ አስተዳደር ስርዓት መፍጠርና ለሰዎች ዝውውር የተቀናጀ ቀጣናዊ ምላሽ መስጠት ላይ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እንደሚገልጹ ተጠቁሟል። ኢጋድ በቀጣናው የሚታየውን መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመራቸውን የጋራ ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመልክቷል። ዜጎች ህጋዊ አማራጮችን እንዲከተሉና የኢኮኖሚ ፈተናን ጨምሮ ለሌሎች ገፊ ምክንያቶች ዘላቂ መፍትሄ መስጠት በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ ገልጿል። ስብሰባው ጥቅምት 10 እና 11 በባለሙያዎች፣ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚኒስትሮች ደረጃ ይካሄዳል።
የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በቁርጠኝነት ሊተገብሩ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት
Oct 19, 2025 385
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የአፍሪካ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) አፈጻጸም ውጤታማነት ለማሳደግ በትኩረት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብስባ ከጥቅምት 11 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎች እና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገም እና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስ እና ዘላቂ የውሃና ተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩ ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚከናውን ኢዜአ ከህብረቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
የብዙዎች ቤት…
Oct 27, 2025 145
እስካሁን በተደረገ የጥናት ውጤት መሠረት ከ81 በላይ የአጥቢ እንስሣት፣ ከ450 በላይ የአዕዋፍ እና ከ400 በላይ የእፅዋት ዝርያዎች መኖሪያ ነው። ከእነዚህ መካከል አምስቱ የአዕዋፍ ዝርያዎች በዚህ ሥፍራ ብቻ ይገኛሉ፤ ከአምስቱ መካከል በተለይም የአንዷ ዝርያ ዓለም አቀፍ የዘርፉ ተመራማሪዎችንና ጎብኚዎች ቀልብ መሳቡ ይጠቀሳል። ከአካባቢው ተፈጥሯዊ አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ጋር መጣጣም የቻሉ የቆላ እፅዋት (ዛፎች) በምቾት በስፋት እንደሚገኙበትም ይገለጻል። የተመሠረተው በ1958 ዓ.ም ሲሆን፤ ስፉቱም 591 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ነው፤ በቁጥርም ሆነ በሥብጥር የብዙዎች መኖሪያ የሆነው ይህ ሥፍራ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ይሰኛል። መንግሥት በሰጠው ትኩረት ከነበረው በተሻለ ሁኔታ እንስሣቱም ሆኑ እፅዋቱ እየኖሩ ነው፤ ከሕገ ወጥ ድርጊትም እንዲጠበቁ ማድረግ መቻሉን የፓርኩ ኃላፊ አደም መሐመድ ለኢዜአ አረጋግጠዋል። በፓርኩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁንም ለ247 ወገኖች ቋሚ እና ለ2 ሺህ 535 ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ባሳለፍነው ዓመትም በ1 ሺህ 751 የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች እንደተጎበኘ ኃላፊው ገልጸዋል።
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 667
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል።   ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው።   የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።   እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።   “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው።   ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል።   ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።   የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
 ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 649
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም።   በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል።   የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል።   በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል።   ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል።   በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።   በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 858
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።  
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1439
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1967
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2805
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2934
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 741
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 548
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6390
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4868
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 55421
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51217
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 31939
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 29446
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 25943
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 24501
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24251
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 24096
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 55421
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 51217
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 31939
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 29446
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
''ቦር ተራራ'' የየሞች የፈውስ ምድር 
Oct 27, 2025 204
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) የም ዞን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ይገኛል። በዞኑ የቦር ተራራ ዋነኛው የመድኃኒት እጽዋት መገኛ እና ምንጭ በመሆኑ የሞች በየዓመቱ ጥቅምት ወርን ጠብቀው በ17ኛው ቀን ከዚህ ተራራ በህብር ሆነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስነ-ስርዓት ያካሂዳሉ፤ ይሰባስባሉም ። የቀደምት የየም አባቶችና እናቶችን በማሳተፍ የሚከወነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ከባህር ጠለል በላይ 2 ሺህ 939 ሜትር ከፍታ ላይ በሚገኘው ቦር ተራራ ላይ ነው። በዚህ ተራራ ላይ በየዓመቱ ጥቅምት 17 ቀን የሞች ለዓመት የሚያገለግላቸውን የመድኃኒት እጽዋት ይለቅማሉ። ተግባሩንም አዋቂዎች በጋራ ሰብሰብ ብለው ለመድኃኒት የሚውለውን ቅጠል በጥሰው፣ ስር ምሰው፣ አስሰውና መርጠው ይሰበስባሉ። ይህም የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስርዓት "ሳሞ ኤታ" ተብሎ ይጠራል ። አያምጣውና ህመም ሲከሰት ታማሚውን ሰው ወይም እንስሳን ከበሽታው ለመፈወስ የተዘጋጀው ባህላዊ መድሃኒት በባህላዊ ሃኪም ትዕዛዝ መሰረት በህመሙ ልክ ይታዘዝለታል። መድሃኒቱን ለመጠቀምም የጠቢባን አባቶችን ፈለግ ተከትሎ መፈፀም የግድ ይላል። የሞች አጅግ አስገራሚ እና አስደናቂ የሆኑ የበርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤት ናቸው ካስባሏቸው እሴቶች መካከል ይህ ለየት ያለው ክዋኔያቸው አንዱ ነው፡፡ አባቶች ታዳጊና ወጣቶችን አስከትለው ወደ ቦር ተራራ በመውጣት የሚፈፅሙት ባህላዊ ክዋኔ በመሆኑም ከትውልድ ወደ ትውልድ ቅብብሎሹን ጠብቆ እስከ አሁን እንዲዘልቅ እድርገውታል።   በየሞች ዘንድ የባህላዊ መድኃኒት አዋቂዎች ከሚባሉት መካከል አንዱ አቶ ጌታቸው ሃይለማርያም፤ የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ልምድን የቀሰሙት ከአባታቸው መሆኑን በመግለፅ አያታቸው ከቅድመ አያቶቻቸው በመውረስ እዚህ እንዳደረሱት ይናገራሉ። የቦር ተራራ ለመድሃኒት ዕፅዋት ለቀማው የተመረጠበትን ምክንያት ሲያስረዱም ቦታው ተራራ በመሆኑ ማንም ያልደረሰባቸው የተለያዩ እፅዋትን ለማግኘት አመቺ ከመሆኑ ጋር ያያይዙታል። በሌላም በኩል ጠዋት ፀሐይ ስትወጣ መጀመሪያ የምታገኘው ተራራውን በመሆኑና ክረምቱ አልፎ ጥቅምት ሲገባ የተለያዩ ቅጠላ ቅጠሎችን በብዛት እና በዓይነት ለማግኘት ተመራጭ ወቅት መሆኑም ቦታው የተመረጠበት ሌላኛው ምክንያት ነው ብለዋል። በጥቅምት 17 ለመድኃኒትነት የሚያገለግለው ዕፅዋት ቅጠልም በየፈርጁ ተለቅሞ እና ተቀምሞ ይቀመጣል ሲሉም አስረድተዋል። የተዘጋጀው ባህላዊ መድኃኒትም ለሰው ልጆችና ለቤት እንስሳት ያገለግላል ሲሉም አስረድተዋል፡፡ ይኸው በዚህ ቀን የተለቀመው የመድኃኒት ዕፅዋት ከዚህኛው ጥቅምት 17 እስከሚቀጥለው ዓመት ጥቅምት 17 ድረስ እንደሚያገለግልም አቶ ጌታቸው አስረድተዋል፡፡ የባህል መድኃኒት ሰብሳቢዎች እና ተጠቃሚዎች ጊዜውን ጠብቀው ከተለያዩ ቦታዎች ወደ ቦር ተራራ እንደሚመጡ የሚገልጹት የባህል መድኃኒት አዋቂው ዛሬ ዛሬ እሳቸውን ጨምሮ መድኃኒት ቤቶችን በመክፈት ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ የባህል መድኃኒቶችን በመሸጥ ኑሯቸውን እየመሩ የሚገኙ አያሌ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉም ይናገራሉ። ሌላኛው የባህል መድኃኒት አዋቂው አቶ ወልደመስቀል ጆርጋ በበኩላቸው በየሞች ዘንድ የተዘጋጀው የመድኃኒት ዕፅዋት ጥቅም ላይ የሚውለው ህመም ሲያጋጥም ብቻ ሳይሆን በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል መሆኑን ጠቁመው መድኃኒቶቹም ብቻቸውን እንዲሁም ከምግብ ጋር በመመገብ ለጥቅም እንደሚውሉም አንስተዋል። የየም ምድር የበርካታ የመድኃኒት ዕፅዋቶች መገኛ አካባቢ " የፈውስ ምድር " ነው የሚሉት ደግሞ በየም ባህላዊ መድኃኒት ዙሪያ ጥናት ያደረጉት በጅማ ዩኒቨርሲቲ የፎክሎር መምህር እና ተመራማሪ ለማ ንጋቱ (ዶ/ር) ናቸው። ከየሞች አያሌ የባህል ዕሴቶች መካከል የባህል መድኃኒት ለቀማና ቅመማ አንዱና ዋነኛው የሀገር በቀል እውቀት ማሳያ መሆኑን ገልፀው የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ስነ-ስርዓቱ ከጥንት ጀምሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ዛሬ ላይ የደረሰ እንደሆነም ያስረዳሉ፡፡   ማህበረሰቡ የራሱንም ሆነ የእንስሳትን ጤና የመጠበቅ የቆየ ባህል ያለው መሆኑን በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው የባህላዊ መድኃኒት ለቀማው ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚሳተፉበት ዓመታዊ ክዋኔ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ሌላው ገራሚው ነገር ይላሉ አጥኚው ታላላቆች ታናናሾቻቸውን አስከትለው የለቀማ ሂደቱን የሚያስረዱበት መንገድ ደግሞ ስርዓቱ ለመጪው ትውልድ እንዲተላለፍ የሚያስችል ትውልድ ተሻጋሪ የሀገር በቀል እውቀት ሽግግር ስርዓት ማሳያ እንደሆነም ነው የገለጹት። በዚህም ሂደት የሚነገሩ ስነ-ቃሎች መሞጋገስ፣ ጭፈራና ደስታ ይስተናገድባቸዋል። ይህም ማህበራዊ ትስስርን ይበልጥ የሚጠናክሩበትን ሁነት የሚፈጥር ስርዓት ነው። የየም ዞን ባህል እና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ሞጋ በበኩላቸው የቦር ተራራ የመጀመሪያውን የማለዳ የፀሐይ ጎህ የሚፈነጥቅበት የንጋት ብርሃን ቀድሞ የሚያገኝ በመሆኑ፥ በዚህ አካባቢ የሚገኙ እጽዋት በሽታን የመከላከልና ፈዋሽነታቸው ከፍተኛ ነው ተብሎ ስለሚታመን ለዚህ ክዋኔ ቦታው መመረጡን ነው የሚገልፁት። ለዚህም ነው የሞች ይህንን ስፍራ ከሌሎች ቦታዎች አስበልጠው የሚወዱት፤ በየዓመቱም ጥቅምት 17 ቀን ወደ እዚህ ስፍራ በማቅናት ለዓመት ፍጆታ የሚያገለግላቸውን መድኃኒትም ይሰበስቡበታል ብለዋል። ጥቅምት 17 በየም ዘንድ ለየት የሚያደርገው ሌላው የመድሃኒት ዕፅዋት ለመልቀም እና ለመጠቀም ብቻ ሳይሆን የለቀማውን ትዕይንት ለመመልከት የሚመጡ ቱሪስቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸው ሌላው ትልቁ ትሩፋት ነው ይላሉ። የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማው ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት በመሆኑ፥ ለአብሮነት እና ሃገር በቀል እውቀት ለመቅሰም ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ነው አቶ መስፍን የገለፁት።    
የአፍሪካ የግብርና፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ፤ እድሎች እና ፈተናዎች
Oct 20, 2025 487
አፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማሳካትና እንድትበለጽግ የጀመረችው ጉዞ ወሳኝ መዕራፍ ላይ ይገኛል። የአህጉሪቱን የመለወጥ ትልም ባሏት እምቅ ተፈጥሯዊ ጸጋዎች ላይ የተመረኮዘ ነው። ተዝቆ የማያልቀው የአፍሪካ ብዝሃ ሀብት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግና አይበገሬ አቅም መገባንት የሚያስችሏትም ጭምር ናቸው። ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ ሀብቶቿ እና ብዝሃ ከባቢ የአየር ንብረቷ ከሀብቶቿ መካከል ይጠቀሳሉ። ግብርና አሁንም የአፍሪካ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው። ዘርፉ ለአህጉሪቱ 35 በመቶ የሚጠጋ አጠቃላይ ጥቅል ሀገራዊ ምርት(ጂዲፒ) አስተዋጽኦ ያደርጋል። 60 በመቶ ህዝብም በግብርና ስራ እንደሚተዳደር የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) ሰነድ ያሳያል። ከዚህም ውስጥ አብዛኞቹ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው።   ሴቶች በግብርናው ዘርፍ ካለው የሰው ኃይል የ50 በመቶ ድርሻው ይወስዳሉ። የአፍሪካ ህዝብ 60 በመቶ ድርሻ የያዘው ወጣት በግብርና ንግድ፣ እሴት መጨመርና የኢኖቬሽን ስራዎች ያለው ተሳትፎ እያደገ መጥቷል። የዓለም 60 በመቶ ያልለማ መሬት ያለው በአፍሪካ ነው። ሰፊ የውሃ ሀብቶችና እያደገ ያመጣው ብሉ ኢኮኖሚ(የባህር እና ሌሎች የውሃ ሀብቶች) ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ እድገትን የሚያረጋግጡ ናቸው። የመሰረተ ልማቶች ተደራሽነት ማደግ፣ ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶችና ኢኖቬሽንን የተመረኮዙ የፋይናንስ አማራጮችን መስፋት ግብርናን የምግብ ምንጭ ብቻ ሳይሆን ለኢንዱስትሪ ልማት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ እና ንግድ መሳለጥ ትልቅ አቅም መሆን ይችላል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና በግብርና ምርቶችና አገልግሎቶች ያለውን አህጉራዊ የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ በማሳደግ ረገድ ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ ነው። የንግድ ቀጣናውን በሚገባ መጠቀም ከተቻለ እ.አ.አ በ2030 የግብርና ንግድ ልውውጡን በ30 በመቶ ማሳደግ እንደሚቻል ጥናቶች ያመለክታሉ። ግብርናው የተጠቀሱት ጥንካሬዎች ያሉት ቢሆንም ረጅም ጊዜ የዘለቁ መዋቅራዊ ፈተናዎች አብረውት ዘልቀዋል። የግብርና ምርቶች ላይ የሚፈለገውን ያህል እሴት አለመጨመር፣ የቴክኖሎጂ አጠቀቃምና የምርታማነት ውስንነት፣ የመሰረተ ልማቶች እና ሎጅስቲክስ በበቂ ሁኔታ አለመሟላት፣ ተቋማዊና አስተዳደራዊ ክፍተቶች ከአየር ንብረት ለውጥና ሌሎች ተፈጥሯዊ አደጋዎች እንዲሁም እያደገ ከመጣው ህዝብ ጋር ተዳምሮ ግብርናውን እየፈተነው ይገኛል።   ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ማጠንጠኛ የሆነው ጉዳይ የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት(ካዳፕ) ነው። እ.አ.አ በ2003 የአፍሪካ ህብረት በሞዛምቢክ ባደረገው ስብሰባ የግብርና የምግብ ዋስትና ድንጋጌን አጽድቋል። ይህ ማዕቀፍ የማፑቶ ድንጋጌ ስያሜን በማግኘት የካዳፕ ትግበራ በይፋ እንዲጀመር አድርጓል። የማፑቶ ድንጋጌ እ.አ.አ በ2014 በማላቦ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025 የተተገበረ) በአዲስ መልክ የታደሰ ሲሆን የተለያዩ ቃል ኪዳኖችን በውስጡ ይዟል። ይህም በካዳፕ አማካኝነት የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ከአጠቃላይ ዓመታዊ ጥቅል ምርታቸው(ጂዲፒ) ቢያንስ ስድስት በመቶውን ለግብርናው ዘርፍ እንደሚመድቡና በየሀገራቱ በዘርፉ በየዓመቱ በአማካይ ስድስት በመቶ እድገትን የማሳካት ግብ አለው። ረሃብን ማጥፋት፣ ድህነትን በግማሽ መቀነስ፣ የማይበገር አቅም መገንባትና የጋራ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ሌሎች ግቦች ናቸው። ካዳፕ የአፍሪካ ሀገራት በስርዓተ ምግብ ያላቸውን ኢንቨስተመንት በማሳደግ፣ በአፍሪካ የእርስ በእርስ የግብርና ንግድን በማሳደግና የፖሊሲ መሰናሰልን በመፍጠር ቁልፍ ሚና ተወጥቷል። ይሁንና የተመዘገቡት ውጤቶች ያልተመጣጠነ ልዩነት የሚታይባቸው ናቸው። የ2023 የካዳፕ የግምገማ ሪፖርት እንደሚያሳየው የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የማላቦ ግቦችን ማሳደግ የሚያስችል መንገድ ላይ እንዳልሆኑ ያስቀምጣል። ይሁንና 26 ሀገራት በተቀመጡ ግቦች መመዘኛ መሻሻል እንዳሳዩ ይገልጻል። ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ካሜሮን፣ ግብጽ፣ ማሊ፣ ጋና እና ጋምቢያ የተሻለ አፈጻጸም ካላቸው ሀገራት መካከል ይጠቀሳሉ። አብዛኞቹ ሀገራት በግብርና ኢንቨስትመንት፣ ምርታማነት እና የፖሊሲ ትግበራ ላይ ፈተናዎች እንዳሉበት ሪፖርቱ አመልክቷል። ሀገራት የሰነዱን ትግበራ ማፋጠንና ተቋማዊ ቅንጅትን ማጠናከር እንደሚገባቸው አሳስቧል።   የማላቦ ድንጋጌ ወደ መገባደዱ ላይ የሚገኝ ሲሆን የካዳፕ ቀጣዩ ምዕራፍ የካምፓላ ድንጋጌ ነው። ይህ የትግበራ ምዕራፍ ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚቆይ ነው። የካምፓላ ድንጋጌ ከማፑቶ እና ማላቦ ድንጋጌዎች ትምህርቶችን በመውሰድ የግብናውን እድገት ማላቅ ግቡ አድርጎ ይዟል። የካምፓላ አጀንዳ ኢኖቬሽን፣ ዲጂታላይዜሽን፣ አረንጓዴ እድገት እና አይበገሬነት ያላቸውን ሚና በማንሳት መስኮቹ ስርዓተ ምግብን ዘላቂና አካታች የማድረግ ግብን ማሳካት እንደሚያስችሉ አመልክቷል። በዚህ ማዕቀፍ እ.አ.አ 2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ህዝብ ይኖራታል ተብሎ የሚጠበቀውን አፍሪካን በራስ አቅም የመመገብ ውጥን የያዘ ነው። ይሁንና የግብርና ምርታማነት ከዓለም አቀፍ አማካይ የምርታማነት ምጣኔ አንጻር ሲታይ አሁንም ወደ ኋላ ቀረት ያለ ነው። ይህም አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች የተገደበ የፋይናንስ አቅርቦት ማግኘታቸው እንዲሁም የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትና የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው አለመደረጉ የችግሩ አብይ መንስኤ ሆኖ ይጠቀሳል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎችና የከባቢ አየር ብክለት ፈተናዎቹ እንዲበረቱ አድርጓል። ዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ የበይነ መንግስታት ፓናል(IPCC) አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እርምጃዎችን በፍጥነት ካልወሰደች እ.አ.አ በ2050 የግብርና ምርታማነቷ ከ20 እስከ 30 በመቶ ሊቀንስ እንደሚችል ገምቷል። ከ250 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ አፍሪካውያን ደህንነቱ ያልተረጋገጠ እና ንጽህናው ያልተጠበቀ የውሃ አቅርቦት ፈተና ውስጥ ይገኛሉ። በህዝብ ቁጥር መጨመር፣ በከተሜነትና ኢንዱስትሪ መስፋፋት ምክንያት ንጹህ የውሃ አቅርቦትን የማግኘት ጉዳይ የበለጠ ሊስፋ እንደሚችል ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩና ፈተናዎች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ለአባል ሀገራት የፋይናንስ እና የቴክኒክ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል። የህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር የስራ ክፍሉ(DARBE) አማካኝነት የአፍሪካን ፖሊሲዎች፣ ፕሮግራሞችና ኢኒሼቲቮች የተናበቡና የጋራ ግብ ያላቸው እንዲሆኑ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል። የአቅም ግንባታ፣ የቴክኒክ እና የፖሊሲ ድጋፍም የሚያደርግ ሲሆን ብሄራዊ እቅዶች ከአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሰነዶችና የአጋርነት ማዕቀፎች ጋር የተጣጠሙ መሆናቸውን ያረጋገጣል። የስራ ክፍሉ ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች ጋር አጋርነቶችን የማጠናከር ስራ ያከናውናል። ግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት እንዲሁም የተፈጥሮ እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በዘላቂነት መጠቀም ላይ የተቀናጁ አሰራሮችን መፍጠር ላይም ይሰራል። የዘርፉ አጠቃላይ ስራዎች አካል የሆነው ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮች፣ ባለሙያዎችና የልማት አጋሮች ይሳተፋሉ። የአፍሪካ የግብርና ኢኒሼቲቮች አፈጻጸም መገምገምና ዘርፉ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከር የስብሰባው አላማ ነው። እ.አ.አ በ2023 በአዲስ አበባ የተካሄደውን አምስተኛው የልዩ ኮሚቴ ስብሰባ ውጤቶች ግምገማ ይደረጋል። የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም(ካዳፕ) የማላቦ ድንጋጌ(ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2025) ስኬቶች እና የካዳፕ የካምፓላ ድንጋጌ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035) አፈጻጸም ላይ ውይይት ይካሄዳል። የስርዓተ ምግብን ማጠናከር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ምርታማነት ስርዓት መዘርጋት፣ የበካይ ጋዞችን ልህቀት መቀነስና ዘላቂ የውሃና የተፈጥሮ ሀብቶች አስተዳደርን ማጠናከር ሌሎች የምክክር አጀንዳዎች ናቸው። በአፍሪካ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ዘላቂ እድገትን ማምጣት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ። ውይይቱ እ.አ.አ በ2026 በአዲስ አበባ የሚካሄዱትን የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባና የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጅ ተመላክቷል። የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር አጀንዳ 2063 ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ዘርፎች መሆናቸውን አመልክቷል። ህብረቱ የግብርና እና የገጠር ልማት የበለጠ ማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም አመልክቷል። የህብረቱ አባል ሀገራት የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራምን በተጠናከረ ሁኔታ እንዲተገብሩም ጥሪ አቅርቧል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ጥቅምት 11 እና 12 እንዲሁም ጥቅምት 14 በሚኒስትሮች ደረጃ እንደሚያከናውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። አፍሪካ ወደ ዘላቂ ግብርና፣ የገጠር ልማት፣ ውሃ አስተዳደር እና አካባቢ ጥበቃ እያደረገች ያለው ጉዞ አንገብጋቢ አጀንዳና ሽግግሩን ለማፋጠን ወሳኝ ሚና አለው። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የፋይናንስ ማነቆ፣ መሰረተ ልማቶች እና የፖሊሲ የመፈጸም አቅም ውስንነትን ጨምሮ የተለያዩ ፈተናዎች ቢኖሩባትም እድሎቿ ፈርጀ ብዙ ናቸው። በርካታ ያልለማ መሬት፣ ሰፊ የውሃ ሀብት፣ ወጣቶች እና የብሉ ኢኮኖሚ ሀብቶች በአፍሪካ ዘላቂ የግብርና እድገት ለማረጋገጥና ሁሉን አቀፍ ስርዓተ ምግብ ለመገንባት የሚያስችል ነው። ለአርሶ አደሮች በቂ የፋይናንስ አቅርቦት ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ አቅማቸውን መገንባት ቁልፍ ጉዳይ ነው። ሀገራት ብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸውን ከአህጉራዊ ማዕቀፎች ጋር ማጣጣም ይኖርባቸዋል። ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋት ይገባል። የተፈጥሮ ሀብትን በሚገባ መጠቀም፣ በኢኖቬሽን ላይ መዋዕለ ንዋይን ፈሰስ ማድረግና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች፣ አረንጓዴ እና የበለጸገች አህጉር መገንባት ይቻላል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም