ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የታክስ አሰራርን በማዘመን ፍትሐዊነትና የሕግ ተገዢነትን ለማረጋገጥ እገዛ ያደርጋል
Jun 10, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡- የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የታክስ አሰራርን በማዘመን ፍትሐዊነትና የሕግ ተገዢነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የአስረጂ መድረክ ተካሂዷል።   የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቃዱ ሆረታ በዚህ ወቅት፤ የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ከኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ጋር የተጣጣመ ዘመናዊ የታክስ አሰራር ለመፍጠር ያስቻላል ብለዋል። በታክስ ከፋዩ ማህበረሰቡ የሚነሱ መሰረታዊ የፍትሐዊና የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችንም መፍትሔ ለመስጠት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል። የመንግሥትን ገቢ የመሰብሰብ አቅም በማጎልበት ተጠያቂነትን ከግልጸኝነት ያጣመረ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት እንደሚያስችልም ተናግረዋል። የምክር ቤቱ አባላትና የሕግ ማዕከል ባለሙያዎችም፤ በማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ የታክስ ስሌት፣ የይርጋ ጊዜ ገደብ፣ የታክስ ከፋይ መስተንግዶና ተያያዥ ጉዳዮችን በማስመልከት ጥያቄ አንስተዋል። በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሕግ አማካሪ ዋሲሁን አባተ፤ በረቂቅ አዋጁ የይርጋ ጊዜው አስር ዓመት ሆኖ መቀመጡ በታክስ ከፋዩ ላይ የሚኖረውን ጫና መቀነስ እንደሚያስችል ተናግረዋል። በገንዘብ ሚኒስቴር የሕግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፈ ተወዳጅ መሐመድ፤ የታክስ ደረሰኝ አለመስጠት ተመሳሳይ የገንዘብ ቅጣት መጣሉ ሆን ተብሎ የሚፈጸምን የታክስ ማጭበርበር በማስቀረትና ደረሰኝ መቁረጥን ባህል ያደርጋል ብለዋል። በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ አማካሪ ያሬድ ፍቃደ በበኩላቸው፤ የገለልተኛ አስማሚ ስርዓት ገለልተኛ ሆኖ የሚቋቋም በመሆኑ ግብር ከፋዩ የሚገጥመውን ችግር መፍቻ ተጨማሪ አማራጭ ነው ብለዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጀ፤ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ኢኮኖሚው በሚያመነጨው ልክ ገቢን ለመሰብሰብና የታክስ አስተዳደርን ለማዘመን እንደሚያስችል ተናግረዋል። በአስረጂ መድረኩ ግልፅ ያልሆኑ ጉዳዮች ይበልጥ ማጥራት የሚያስችል ማብራሪያ መሰጠቱን ጠቁመው የተደረጉት ማሻሻያዎች ፍትሐዊነትንና የሕግ ተገዢነትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።  
አበረታች ቅመሞች የመጠቀም ወንጀልን ለመከላከል የፍትህ አካላት ቅንጅታዊ አስተዋጾ ወሳኝ ነው
Jun 10, 2026 93
አዳማ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ አበረታች ቅመሞች የመጠቀም ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የፍትህ አካላት አስተዋጾ ወሳኝ መሆኑን የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ ከፌዴራል ፖሊስ እና ከፍትህ አካላት ጋር ወንጀሉን በቅንጅት የመከላከል ሥራውን ውጤታማ ለማድረግ ያለመ የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል።   የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን ይደርሳል በወቅቱ እንደገለጹት፤ የተቀናጀ የፀረ-አበረታች ቅመሞች መከላከልና መቆጣጠር ሥራ የዜጎችን ሁለንተናዊ ደህንነት ለመጠበቅ የሚደረገው ጥረት አንዱ አካል ነው። አበረታች ቅመሞችን መጠቀም በህግ የተከለከለ የወንጀል ተግባር በመሆኑ፣ ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የፍትህ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን አመልክተዋል። የውይይት መድረኩም የፀጥታና የፍትህ አካላት ከባለስልጣኑ ጋር በቅንጅትና በትብብር እንዲሰሩ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል። "ድርጊቱ የአትሌቲክስ ዘርፉን ከመጉዳት ባለፈ በሀገር ገፅታ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድር በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር መስራት አስፈልጓል" ብለዋል። ባለፉት ዓመታት የህግ ማዕቀፎችን ከማውጣትና የባለድርሻ አካላትን ትብብር ከማጠናከር አንጻር አመርቂ ሥራዎች እንደተሰሩ የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ይህን ለማስቀጠል ቅንጅታዊ ሥራን ይበልጥ ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ድርጊቱ በስፖርተኞች ላይ የስነ-ልቦና ጫና ከመፍጠር ባለፈ የተወዳዳሪነት አቅምን የሚፈታተን ወንጀል በመሆኑ መከላከሉና መቆጣጠሩ የጋራ ሃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት የባለስልጣኑ የውጤት አስተዳደርና ህግ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ንጋቱ መኮንን እንዳሉት፤ አበረታች ቅመሞችን የመጠቀም የህግ ጥሰቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መጥተዋል። እስካሁን እየተወሰዱ ያሉ የህግ እርምጃዎች በሚፈለገው ደረጃ ባለመሆናቸው ችግሩን ከመፍታት አኳያ ክፍተቶች እንደነበሩ አስታውሰዋል። ችግሩን ለመፍታት የፀረ-አበረታች ቅመሞች ህግ ማዕቀፎች በተግባር ላይ ውለው ውጤታማ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተቀናጀ መልኩ መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤና የቴክኖሎጂ ውድድር ከፊታችን አርብ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Jun 10, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤና የቴክኖሎጂ ውድድር ከመጪው አርብ ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያካሂደውን ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ እና የቴክኖሎጂ ውድድር በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።   የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ሙሉጌታ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ኢንስቲትዩቱ በምርምርና በቴክኖሎጂ ልማት ረገድ በርካታ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ይህ ዓለም አቀፋዊ የምርምር ጉባዔ እና የቴክኖሎጂ ውድድርም፤ ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ የጀመራቸውን የፈጠራና የምርምር ስራዎች ይበልጥ አጠናክሮ እንዲቀጥል ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን ይህንን ጉባኤ በስኬት ለማካሄድ ተቋሙ በቂ ዝግጅት ማድረጉንም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። ዓለም አቀፋዊ የምርምር ጉባዔ እና የቴክኖሎጂ ውድድርም ከሰኔ 5 እስከ 7 2018 ዓ.ም የሚቆይ እንደሚሆን አመልክተዋል፡፡ በጉባኤው ከ 16 አገራት የተወጣጡ ተመራማሪዎች እና ሌሎች አካላት የሚሳተፉ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
አመራሩ ወቅቱን የዋጀ ዕውቀትን በመታጠቅ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ይጠበቅበታል
Jun 10, 2026 82
ደሴ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፡-አመራሩ ወቅቱን የዋጀ ዕውቀትን በመታጠቅና እንደ አስቻይ ሁኔታው በመምራት መሰረታዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚገባ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ አመለከቱ። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ አካዳሚክ ስታፍ ሰራተኞችና ለካውንስል አባላት ስልጠና እየሰጡ ነው።   አቶ ዛዲግ በስልጠናው ላይ እንዳሉት፤ አመራሩ ወቅቱን የዋጀ ዕውቀትን በመታጠቅ መሰረታዊ ለውጥ ማስመዝገብ ይጠበቅበታል ብለዋል። በተለመደውና ከዚህ ቀደም በነበሩ አሰራሮች መቀጠል ወቅቱ እንደማይፈቅድ ያስገነዘቡት አቶ ዛዲግ ከዘመኑ ጋር እኩል በመራመድና በመስራት በየዘርፉ ለውጥ ማምጣት አስፈላጊ ነው ያሉት። የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ አመራሩ የዓለምን ተለዋዋጭ ባህሪና ሁኔታ ተረድቶ በመምራት ውጤታማ መሆን እንዲችል ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በዚህም ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለአመራሩ፣ ለአካዳሚክ ስታፍ ሰራተኛውና ለካውንስል አባላት ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው በዚህም አቅምን በማጎልበት ውጤታማ ተግባር ማከናወን ይገባል ብለዋል።   እንዲሁም አውቆና ወቅቱን ተረድቶ በመስራት ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ከመፍጠር ባለፈ አቅላይ የፈጠራ ስራዎችን ማብዛት እንደሚገባም አመልክተዋል። ዩኒቨርሲቲው በተግባር ተኮር ትምህርት ብቁ ትውልድ ከመፍጠር ባለፈ ቴክኖሎጂ ላይ አተኩሮ በመስራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አክለዋል። ወቅቱን በዋጀ ክህሎትና እውቀት ተመርተን ውጤታማ ተግባር ለማስመዝገብ ስልጠናው ያግዘናል ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የዓለም አቀፍ ግንኘነትና አጋርነት ትብብር ዳይሬክተር አስረሴ ሞላ (ዶ/ር) ናቸው። ስልጠናውን በንቃት በመከታተል መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት እንደሚሰሩም ገልጸዋል። ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ላይም አመራሮች፣ የአካዳሚክ ስታፍ ሰራተኞች፣ የካውንስል አባላትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
የሚታይ
የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jun 10, 2026 190
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታወቁ። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት ስኬት በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን ማስፈን የሚያስችል ተምሳሌታዊ አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሀገር አቀፍና የክልል ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ቀረጻ ግብዓት ማሰባሰቢያ የውይይት መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል።   የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፤ ኮሚሽኑ ያከናወናቸውን ተግባራትና የእስካሁን ሂደቶችን በማስመልከት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ፣ የተሳታፊ ልየታና ዋናውን የምክክር ጉባኤ የማካሄድ ዝግጅት ስኬታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያንና ባለድርሻ አካላት በእስካሁኑ ሂደት የነበራቸው ንቁ ተሳትፎም ነጻና ገለልተኛ ሀገራዊ ምክክርን ማስተባበር የሚያስችል አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራውም በታላላቅ ህዝባዊ መድረኮች በቀጥታና በጥናት ለኮሚሽኑ ቀርበው የማሰባሰብ ሥራ በስፋት መከናወኑን አብራርተዋል። በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የነበረው የህዝብና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎም ለሚሰሩ ሥራዎች ጥልቅ መነሻ የሚሆኑ የሀገር ሃብቶች መሆናቸውን አስረድተዋል። በዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ሃሳብ የሚሰጡና የሚሳተፉ ተወካዮች በሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች የማስመረጥ ስራ 93 በመቶ መፈጸም እንደተቻለ አስገንዝበዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ አካታችነት፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎም ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወሳኝ ምዕራፍ መሰረት መጣሉን አንስተዋል። የዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረጻ ዝግጅት የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የእስካሁኑ ሂደት ጉልህ ተሳትፏቸውን እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የእስካሁኑ ሂደት አካታች፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊነትም ተምሳሌታዊ የምክክር አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ አስገንዝበዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የሁለት ሀገራት አምባሳደሮችን አሰናበቱ
Jun 10, 2026 302
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡- የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የሉክሰምበርግ አምባሳደር ዣን ክራውዘር እና የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች አምባሳደር መሐመድ ሳሌም አልራሺዲን አሰናብተዋል። በሀገራቱ መካከል ያለው ፍሬያማ እና ስኬታማ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል።   አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት ተሰናባቿ በኢትዮጵያ የሉክሰምበርግ አምባሳደር ዣን ክራውዘር፤ በቆይታቸው የሀገራቱን የዲፕሎማሲ ትብብር የሚያጠናክሩ ሥራዎችን መስራታቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያና ሉክሰምበርግን የኢኮኖሚ ትብብር ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተከናወኑ ተግባራትም ስኬታማ እንደሆኑ አንስተዋል። በዚህም የፋይናንስና ኢኮኖሚ ሙያተኞችን አቅም የሚያጎለብት የስልጠና መርሃ ግብር በመቅረጽ በሁለቱ ሀገራት ውጤታማ የልምድ ልውውጥ መደረጉን አስረድተዋል።   የሀገራቱ ጠንካራ ወዳጅነት ወደፊትም በአረንጓዴ ኢኮኖሚና በፋይናንስ ልማት የትብብር ዘርፎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነታቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የሉክሰምበርግ ኩባንያዎችን ቀልብ በመሳብ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። የሉክሰምበርግ ኩባንያዎችም የኢትዮጵያን የገበያና የኢንቨስትመንት አማራጭ የለውጥ ሂደት በመመልከት ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በሲዳማ ክልል ለሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፈተናዎች ዝግጅት ተደርጓል
Jun 10, 2026 221
ሀዋሳ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ለሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፈተናዎች አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ በየነ በራሳ ገለጹ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ በራሳ የተደረገውን የቅድመ ዝግጅት በማስመልከት ከኢዜአ ጋር ቆይታ አደርገዋል። በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ 26 ሺህ 735 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና እንደሚወስዱ ገልጸዋል። በፈተናው የተማሪዎችን ውጤታማነት ለማሳደግ አስፈላጊ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን ገልጸው፤ የትምህርት ዓመቱ ከመጀመሩ ሁለት ወራት አስቀድሞ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የማዘጋጀት ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል። ዘንድሮ በክልሉ ከሚፈተኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል 50 ከመቶ የሚሆኑት ፈተናውን በበይነ መረብ እንደሚወስዱ ገልጸው፤ ለዚህም ኮምፒውተርን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችን የማሟላት ስራ ተከናውኗል ብለዋል። በተመሳሳይ የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችም ዘንድሮ በተለየ ሁኔታ በመፈተኛ ማዕከላት ፈተናውን እንደሚወስዱ ጠቁመው፤ ይህም ኩረጃን ለመከላከል እና ምቹ የፈተና አስተዳደር ሥርዓት እንዲኖር ያግዛል ብለዋል። በሦስቱም የትምህርት እርከኖች የሚፈተኑ የክልሉ ተማሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ከመደበኛ የትምህርት ሰዓት ውጪ የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲወስዱ መደረጉን ተናግረዋል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ተማሪዎችን በተለያየ መንገድ በመደገፍ ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ግብ ተይዞ ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል። የሃዋሳ አዲስ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ትእዛዙ ባንዳው፤ በትምህርት ቤቱ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚወስዱ ከ420 በላይ ተማሪዎችን ለፈተና ሲያዘጋጁ መቆየታቸውን ገልጸዋል። መምህራን በማጠናከሪያ ትምህርት ተፈታኝ ተማሪዎችን የማብቃት ሥራ ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፤ ሞዴል ፈተናዎችን በመስጠት ፈተናን የማለማመድ ሥራ መሰራቱንም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅተም ተማሪዎችን በበይነ መረብ ለማስፈተን የሚያስችሉ ዝግጅቶችን ከማድረግ ጎን ለጎን ተፈታኞችን በስነ ልቦና የማዘጋጀት ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከሃዋሳ አዲስ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ሃሚዲ የሱፍ እና አዲስ ላቀው፤ በግላቸው ባደረጉት ጥረትና በትምህርት ቤቱ ድጋፍ ለፈተናው መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የማጠናከሪያ ትምህርት፣ ሞዴል ፈተናዎችንና በበይነ መረብ ፈተና መውሰድ የሚያስችላቸውን የቴክኖሎጂ ድጋፍ ማግኘታቸውን ገልጸው፤ በፈተናው የተሻለ ውጤት ለማምጣት መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል።
የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው
Jun 10, 2026 275
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ ገለጹ። በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በ21 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የመስኖ ስንዴ ሰብል ስብሰባ ተጀምሯል።   በዚሁ ጊዜ ምከትል ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት የበጋ መስኖ ሰብል ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እያገዘ ይገኛል። በኦሮሚያ ክልል እየተከናወነ የሚገኘው የበጋ መስኖ ልማት ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም የአርሶ አደሩን ገቢ በዕጥፍ እያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል። የልማት ስራው ግብርናውን ለማሸጋገር ጭምር እያገዘ መሆኑን ጠቅሰው የግብርና ሜካናይዜሽን ግብዓቶችን በብዛት፣ በጥራት እንዲሁም ፈጠራን መጠቀም እያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ኢኒሼቲቭ መልክ እየተካሄደ ሲሆን ይህም በክረምት ዝናብ ብቻ ተወስኖ የነበረው የግብርና ባህል መለወጥ እያስቻለ ነው ብለዋል።   በዚህ ወቅት የክልሉ አርሶ አደር በሁሉም የልማት ወቅቶች የግብርና ስራን እያከናወነ ሲሆን የገጠር ልማትን ከመሠረቱ ለመቀየር የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ነው ያሉት። አቶ አወሉ አብዲ አክለውም በዞኑ በትራክተር ማረስና በኮምባይነር ሰብል የመሰብሰብ ባህል እየተለመደ መጥቷል ብለዋል።
ተቋሙ አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና ምቹ የሚያደርጉ በርካታ የዲጂታላይዜሽን ስራዎችን እያከናወነ ነው
Jun 10, 2026 348
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሰራሩን ዘመናዊ ከማድረግ ባለፈ የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና ምቹ የሚያደርጉ በርካታ የዲጂታላይዜሽን ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡ ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን በበይነ-መረብ ለተፈታኞች ማድረስ የሚያስችል አቅም መፈጠሩንም አመልክተዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ይፋ የተደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በሀገሪቱ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ላይ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎ በቅርቡ ይፋ ሆኖ በትግበራ ላይ የሚገኘው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂም ሀገሪቱን በዲጂታል ዘርፍ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ሰፊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል ግንባታ ዘርፍ እያከናወነችው ባለው ተግባር ዘርፈ-ብዙ ስኬቶች እየተመዘገቡበት ነው፡፡ ኢትዮጵያ በምታደርገው በዚህ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ተቋማቸው የራሱን ሚና ለመጫወት አሰራሩን በቴክኖሎጂ የመቃኘት ሰፊ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህም ተቋሙ የሚሰጣቸውን ልዩ ልዩ አገልግሎቶች ዘመኑን የዋጁ ለማድረግ እየተቻለ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትግበራ ወቅት የተለያዩ ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን በአብዛኛው በበይነ-መረብ ለተፈታኞች ማድረስ የሚያስችል አቅም መፈጠሩን አመልክተዋል። ከተፈታኞች ባሻገር ሌሎች አገልግሎት ፈላጊዎችም ከተቋሙ ድረ-ገጽና የበይነ-መረብ መተግበሪያዎች ጋር ተያያዥ የሆኑ ምቹ አሰራሮች መዘርጋታቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ዜጎች በአካል ወደ ተቋሙ መምጣት ሳይጠበቅባቸው ባሉበት ቦታ ሆነው፤ የጠፋባቸውን ወይም የተበላሹባቸውን የትምህርት ማስረጃዎች ማመልከትና ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ ማግኘት የሚችሉበት አሰራር መፈጠሩን አብራርተዋል። በተጨማሪም የትምህርት ማስረጃ ማጣራት ጥያቄዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መንገድ ምላሽ እንዲያገኙ መደረጉን ገልጸዋል። ተቋሙ በቀጣይም ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር አብሮ ለመራመድና ለዜጎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ቴክኖሎጂን የማላመድና አቅምን የማሳደግ ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። ይህም ማህበረሰቡ ከዲጂታላይዜሽን ተጠቃሚ እንዲሆንና የተቋሙ አገልግሎት ተደራሽነት ይበልጥ እንዲሰፋ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት አመልክተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jun 10, 2026 190
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታወቁ። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት ስኬት በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን ማስፈን የሚያስችል ተምሳሌታዊ አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሀገር አቀፍና የክልል ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ቀረጻ ግብዓት ማሰባሰቢያ የውይይት መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል።   የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፤ ኮሚሽኑ ያከናወናቸውን ተግባራትና የእስካሁን ሂደቶችን በማስመልከት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ፣ የተሳታፊ ልየታና ዋናውን የምክክር ጉባኤ የማካሄድ ዝግጅት ስኬታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያንና ባለድርሻ አካላት በእስካሁኑ ሂደት የነበራቸው ንቁ ተሳትፎም ነጻና ገለልተኛ ሀገራዊ ምክክርን ማስተባበር የሚያስችል አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራውም በታላላቅ ህዝባዊ መድረኮች በቀጥታና በጥናት ለኮሚሽኑ ቀርበው የማሰባሰብ ሥራ በስፋት መከናወኑን አብራርተዋል። በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የነበረው የህዝብና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎም ለሚሰሩ ሥራዎች ጥልቅ መነሻ የሚሆኑ የሀገር ሃብቶች መሆናቸውን አስረድተዋል። በዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ሃሳብ የሚሰጡና የሚሳተፉ ተወካዮች በሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች የማስመረጥ ስራ 93 በመቶ መፈጸም እንደተቻለ አስገንዝበዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ አካታችነት፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎም ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወሳኝ ምዕራፍ መሰረት መጣሉን አንስተዋል። የዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረጻ ዝግጅት የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የእስካሁኑ ሂደት ጉልህ ተሳትፏቸውን እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የእስካሁኑ ሂደት አካታች፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊነትም ተምሳሌታዊ የምክክር አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ አስገንዝበዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የሁለት ሀገራት አምባሳደሮችን አሰናበቱ
Jun 10, 2026 302
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡- የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የሉክሰምበርግ አምባሳደር ዣን ክራውዘር እና የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች አምባሳደር መሐመድ ሳሌም አልራሺዲን አሰናብተዋል። በሀገራቱ መካከል ያለው ፍሬያማ እና ስኬታማ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል።   አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት ተሰናባቿ በኢትዮጵያ የሉክሰምበርግ አምባሳደር ዣን ክራውዘር፤ በቆይታቸው የሀገራቱን የዲፕሎማሲ ትብብር የሚያጠናክሩ ሥራዎችን መስራታቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያና ሉክሰምበርግን የኢኮኖሚ ትብብር ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተከናወኑ ተግባራትም ስኬታማ እንደሆኑ አንስተዋል። በዚህም የፋይናንስና ኢኮኖሚ ሙያተኞችን አቅም የሚያጎለብት የስልጠና መርሃ ግብር በመቅረጽ በሁለቱ ሀገራት ውጤታማ የልምድ ልውውጥ መደረጉን አስረድተዋል።   የሀገራቱ ጠንካራ ወዳጅነት ወደፊትም በአረንጓዴ ኢኮኖሚና በፋይናንስ ልማት የትብብር ዘርፎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነታቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የሉክሰምበርግ ኩባንያዎችን ቀልብ በመሳብ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። የሉክሰምበርግ ኩባንያዎችም የኢትዮጵያን የገበያና የኢንቨስትመንት አማራጭ የለውጥ ሂደት በመመልከት ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ
Jun 10, 2026 502
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በሀገሪቱ ታሪክ ለረጅም ጊዜ ያገለገሉ መሪ በመሆናቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በመልዕክታቸውም ታላቅ ወንድሜ እና ውድ ወዳጄ ናሬንድራ ሞዲ፣ የዓለማችንን ትልቁን እና እጅግ ንቁ የሆነውን የዲሞክራሲ ማህበረሰብ ዘላቂ እምነት በማግኘት፣ ህንድን በራዕይ እና በቁርጠኝነት በተከታታይ ሶስት የዲሞክራሲያዊ የስልጣን ዘመናት በመምራት ላስመዘገቡት ታሪካዊ ስኬት የተሰማኝን ደስታ እገልጻለሁ ብለዋል። የእርሳቸው አመራር በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን ከድህነት ያወጣ፣ የዲጂታል ሕዝባዊ መሰረተ ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ያስፋፋ እና ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ የመሰረተ ልማት እድገትን በማምጣት ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ያስገኘ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በተከታታይነት ለደቡቡ የዓለም ክፍል (Global South) ጠንካራ ድምጽ በመሆን አገልግለዋል ሲሉም ገልጸዋል።
የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ይገኛል
Jun 9, 2026 1763
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ ከሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ክልሎች መካከል የ816 ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። ከዚህም መካከል የ24 የምርጫ ክልሎች ውጤቶች በቦርዱ ተረጋግጠው መጽደቃቸውም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በሰጡት መግለጫ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደው ልዩ ምርጫ መጠናቀቁንም ገልጸዋል። ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1ሺህ 139 ምርጫ ክልሎች ውስጥ ከሁለቱ ምርጫ ክልሎች በስተቀር በሁሉም የጊዜያዊ ውጤት መለጠፉን ገልጸዋል። በሀላባ አንድ እና በቀብሪ በያ ምርጫ ክልሎች ከምርጫ ጣቢያዎች ቦታ ርቀት የተነሳ የመደመር ስራ በምርጫ ክልል ደረጃ አለመጠናቀቁን ገልጸዋል። እስከ አሁን ባለው ሂደት የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤት በማዕከል ደረጃ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ሲሆን፤ የ24 ምርጫ ክልሎች ውጤት መጽደቁን አስታውቀዋል። የ501 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ላይ ከተካሄደው ውስጥ 353 በማዕከል ደረጃ መግባቱን ገልጸው፤ በክልል ምክር ቤት ከ638 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 463 ወደ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል።
በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎች ዛሬ ድምጻቸውን ሰጥተዋል - ምርጫ ቦርድ
Jun 9, 2026 1230
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች ለመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ድምጽ መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደውን ምርጫ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ቦርዱ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በመደበኛው ጠቅላላ ምርጫ በልዩ ሁኔታ ላልተሳተፉ ዜጎች የድምጽ መስጫ ቀን እንደሚያመቻች ገልጸዋል። ቦርዱ ለዚሁ የሚሆን ልዩ የምርጫ ጣቢያ በማዘጋጀት የተለያዩ ስራዎችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። ለአስፈጻሚዎች እና ለአስተባባሪዎች ስልጠና መስጠቱን ገልጸው፤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማድረጉንም ተናግረዋል። ምርጫውን ለማካሄድም በእነዚህ የምርጫ ጣቢያዎች በትላንትናው እለት የምርጫ ቁሳቁስ ሙሉ በሙሉ መቅረቡን ተናግረዋል። በካምፖች በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ሰዓትም በሁሉም ወታደራዊ ካምፖች እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ መጠለያዎች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሲካሄድ የቆየው ምርጫ ከአንድ ጣቢያ ውጪ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ገልጸው፤ በድምጽ አሰጣጥ ሂደቱም ያጋጠመ ችግር እንደሌለ ጠቁመዋል።
በአፋር ክልል በሚገኙ ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች ድምፃቸውን እየሰጡ ነው
Jun 9, 2026 978
ሰመራ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በሚገኙ ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች ድምፃቸውን እየሰጡ መሆኑን በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኀላፊ ጣሃ ዓሊ ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለያዩ ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ወይም በልዩ ሁኔታዎች በታቀደው መደበኛ የድምፅ መስጫ ቀን መሳተፍ ላልቻሉ ዜጎች የተራዘመ ወይም ልዩ የድምፅ መስጫ ቀን ያመቻቻል። ይህ አሠራር ማንኛውም ድምፅ የመስጠት መብት ያለው ዜጋ ከዴሞክራሲያዊ ሂደቱ እንዳይገለልና የምርጫው አካታችነት እንዲረጋገጥ ይረዳል። ቦርዱ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ልዩ የድምፅ መስጫ ቀናትን በማመቻቸት ዜጎች ድምጽ እንዲሰጡ ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህም መሰረት በሀገር ውስጥ በሚገኙ መጠለያዎችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም ዜጎች ድምፅ እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል።   በዚህ ጉዳይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኀላፊ ጣሃ ዓሊ እንደገለጹት፤ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ዛሬ ድምጽ እየተሰጠ ነው። መራጭ ዜጎችም ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በክልሉ ባሉ 19 ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምጽ እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። በዱብቲ፣ ገዋኔ፣ አሚባራና ገለአሎ ምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ አስራ ዘጠኝ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እየተካሄደ መሆኑንም አስታውቀዋል። በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎቹ የሚገኙ ዜጎችም ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም የሚፈልጉትን ፓርቲ በመምረጥ ላይ እንደሚገኙ አቶ ጣሃ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበር ጉዳይ ላይ አቋማችን የጸና ነው-የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jun 9, 2026 930
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበርና ሉዓላዊነቷን የማስጠበቅ ጉዳይ ላይ አቋማችን የጸና ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ታሪክ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም የተቃረኑ ባንዳዎች ሁሉ ከስመዋል፤አሁን ያሉትም የሚገጥማቸው ዕጣ ፈንታ ተመሳሳይ ይሆናል ብለዋል። የሀገርን ሉዓላዊነት ማስከበር፣የግዛት አንድነትን መጠበቅ እና የውስጥ ሰላምን ማስፈን እንደ ዋና ብሔራዊ ጥቅም የሚወሰድ መሆኑ ይታወቃል። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንኑ ለማስከበር እና ለማስጠበቅ በቁርጠኝነት እየሠራ ይገኛል። በአንድ ወቅት የባሕር በር የነበራት ኢትዮጵያ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የባሕር በር እንድታጣ የተደረገበት ሁኔታ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል። በዚህ ረገድ መንግሥት ጠንካራ የዲፕሎማሲ ጥረት እያደረገ ሲሆን ዜጎችም መሠረታዊ አጀንዳቸው አድርገውት ለምላሹ እየተሠራ መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ በተቃራኒ አንዳንዶች ከባዕዳን ጋር በመሰለፍ በባንዳነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን የሚጻረሩ እንዳሉ የሚታወቅ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ በኢትዮጵያ ታሪክ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በመቃረን የሚቆሙ ባንዳዎች መኖራቸውን አስታውሰዋል። እነዚህ አካላት የከሰሙ መሆኑን አንስተው፥ አሁን ያሉትም የሚገጥማቸው ዕጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊ እና የኢዜማ ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ታሪኩ ድንበሩ፤ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ለድርድር የሚቀርብ መሆን የለበትም ብለዋል። በመሆኑም ሁላችንም የሀገር ሰላምን በጋራ የመጠበቅ፣ የኢኮኖሚ ልማት ሥራዎችን በጋራ ማስቀጠል እና ከውጭ የሚቃጡ ጥቃቶችን በጋራ የመመከት ግዴታ አለብን ብለዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበርና ሉዓላዊነቷን የማስጠበቅ ጉዳይ ላይ የሁላችንም አቋማችን የጸና ነው ሲሉ ተናግረዋል። የነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ኡመር አብዱራህማን፤ የትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ የሚፎካከረው ከምንም በላይ ለሀገር እና ለሕዝብ ጥቅም ለመሥራት መሆን አለበት ብለዋል። ከዚህ በተቃራኒ በመቆም በሀገር ብሔራዊ ጥቅምና በዜጎች ደኅንነት ላይ መሥራት የባንዳነት ተግባር ስለመሆኑ ተናግረዋል። የሕዳሴ ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ሱራፌል እሸቱ፤ የትኛውም የፖለቲካ ተዋናይ ይሁን ዜጋ በብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ የተለየ አቋም መያዝ ተገቢነት የሌለው መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በመሆኑም የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ጨምሮ ሌሎችም ኢትዮጵያን በሚመለከቱ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ አቋማችን የጸና እና የማይናወጥ ነው ብለዋል።
የሀገራችንን ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን በመጠቀም ድምፃችንን ሰጥተናል-የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አባላት
Jun 9, 2026 912
ሰመራ፣ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ) የሀገራችንን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን፣ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን በመጠቀም ድምፃችንን ሰጥተናል ሲሉ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አባላት ገለፁ። በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ ማንኛውም መራጭ ድምፅ ለመስጠት በሚኖርበት ወይም በቋሚነት በሚሠራበት አካባቢ ተመዝግቦ መምረጥ እንዳለበት ይደነግጋል። ሆኖም ግን፣በተለያዩ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ምክንያቶች የተፈናቀሉ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች ውስጥ የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩበት ሁኔታ ይፈጠራል። ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን ያደራጃል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም በልዩ ሁኔታ ላይ ባሉ በሀገር ውስጥ መጠለያ ሊሚገኙና በመከላከያ ካምፖች ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ በመካሄድ ላይ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የሰሜን ምስራቅ ዕዙ አባላት እንዳሉት፥ ሰራዊቱ በታላቅ ጀግንነት የሀገሩን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር በማስከበር ላይ ይገኛል። ከዚህ ጎን ለጎን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ለሀገር ይበጃል ላሉት ፓርቲ ድምፃቸውን ሰጥተዋል።   አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል የሰሜን ምሰራቅ ዕዝ ኦዲት ኀላፊ ተወካይ ሻለቃ ንጋቱ ኩምሳ፤ ሰራዊቱ በላቀ ጀግንነት የሀገሩን ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን በዛሬው ዕለት በመምረጡ ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል። በቀጣይነትም በምርጫው ካሸናፊው ፓርቲ ጎን በመሆን የኢትዮጵያን ሰላም የማረጋገጥ፣ ዳር ድንበርን በቆራጥነት የማስከበር ሚናችንን እንወጣለን ብለዋል።   ሻለቃ ባሻ አባተ አርሲኖ በበኩላቸው፤ የተሰጠንን ሀገራዊ ግዳጅ ለመወጣትና የሀገራችንን ዳር ድንበር ለማስከበር የምንጊዜም ዝግጁነታቸውን ገልፀው፤ ከዚሁ ጎን ለጎን በምርጫው መሳተፍ በመቻላቸው እንዳስደሰታቸው ነው ያስረዱት። በምርጫው በመሳተፋቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው፤ ይህም ለሶስተኛ ጊዜያቸው መሆኑንም ተናግረዋል።   መቶ ዓለቃ ኢያሱ ጩማ፤ የሀገሬን ዳር ድንበር እያስከበርኩ በዚህ ወቅት ዴሞክራሲያዊ መብቴን ተጠቅሜ መምረጥ በመቻሌ ደስተኛ ነኝ ብለዋል።   7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በነፃነት መምረጥ መቻላቸውን የተናገሩት ደግሞ አስር ዓለቃ ታመነ ተሻለ ናቸው። የሀገሬን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር እየጠበቅኩና ሰላሟን እያስቀጠልኩ ከዚህ ጎን ለጎን መምረጥ በመቻሌ ደስ ብሎኛል ብለዋል።  
ፖለቲካ
የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jun 10, 2026 190
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታወቁ። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት ስኬት በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን ማስፈን የሚያስችል ተምሳሌታዊ አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሀገር አቀፍና የክልል ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ቀረጻ ግብዓት ማሰባሰቢያ የውይይት መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል።   የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፤ ኮሚሽኑ ያከናወናቸውን ተግባራትና የእስካሁን ሂደቶችን በማስመልከት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ፣ የተሳታፊ ልየታና ዋናውን የምክክር ጉባኤ የማካሄድ ዝግጅት ስኬታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያንና ባለድርሻ አካላት በእስካሁኑ ሂደት የነበራቸው ንቁ ተሳትፎም ነጻና ገለልተኛ ሀገራዊ ምክክርን ማስተባበር የሚያስችል አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራውም በታላላቅ ህዝባዊ መድረኮች በቀጥታና በጥናት ለኮሚሽኑ ቀርበው የማሰባሰብ ሥራ በስፋት መከናወኑን አብራርተዋል። በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የነበረው የህዝብና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎም ለሚሰሩ ሥራዎች ጥልቅ መነሻ የሚሆኑ የሀገር ሃብቶች መሆናቸውን አስረድተዋል። በዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ሃሳብ የሚሰጡና የሚሳተፉ ተወካዮች በሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች የማስመረጥ ስራ 93 በመቶ መፈጸም እንደተቻለ አስገንዝበዋል። የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ አካታችነት፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎም ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወሳኝ ምዕራፍ መሰረት መጣሉን አንስተዋል። የዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረጻ ዝግጅት የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የእስካሁኑ ሂደት ጉልህ ተሳትፏቸውን እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የእስካሁኑ ሂደት አካታች፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊነትም ተምሳሌታዊ የምክክር አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ አስገንዝበዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የሁለት ሀገራት አምባሳደሮችን አሰናበቱ
Jun 10, 2026 302
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡- የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የሉክሰምበርግ አምባሳደር ዣን ክራውዘር እና የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች አምባሳደር መሐመድ ሳሌም አልራሺዲን አሰናብተዋል። በሀገራቱ መካከል ያለው ፍሬያማ እና ስኬታማ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል።   አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት ተሰናባቿ በኢትዮጵያ የሉክሰምበርግ አምባሳደር ዣን ክራውዘር፤ በቆይታቸው የሀገራቱን የዲፕሎማሲ ትብብር የሚያጠናክሩ ሥራዎችን መስራታቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያና ሉክሰምበርግን የኢኮኖሚ ትብብር ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተከናወኑ ተግባራትም ስኬታማ እንደሆኑ አንስተዋል። በዚህም የፋይናንስና ኢኮኖሚ ሙያተኞችን አቅም የሚያጎለብት የስልጠና መርሃ ግብር በመቅረጽ በሁለቱ ሀገራት ውጤታማ የልምድ ልውውጥ መደረጉን አስረድተዋል።   የሀገራቱ ጠንካራ ወዳጅነት ወደፊትም በአረንጓዴ ኢኮኖሚና በፋይናንስ ልማት የትብብር ዘርፎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነታቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የሉክሰምበርግ ኩባንያዎችን ቀልብ በመሳብ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። የሉክሰምበርግ ኩባንያዎችም የኢትዮጵያን የገበያና የኢንቨስትመንት አማራጭ የለውጥ ሂደት በመመልከት ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ
Jun 10, 2026 502
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በሀገሪቱ ታሪክ ለረጅም ጊዜ ያገለገሉ መሪ በመሆናቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በመልዕክታቸውም ታላቅ ወንድሜ እና ውድ ወዳጄ ናሬንድራ ሞዲ፣ የዓለማችንን ትልቁን እና እጅግ ንቁ የሆነውን የዲሞክራሲ ማህበረሰብ ዘላቂ እምነት በማግኘት፣ ህንድን በራዕይ እና በቁርጠኝነት በተከታታይ ሶስት የዲሞክራሲያዊ የስልጣን ዘመናት በመምራት ላስመዘገቡት ታሪካዊ ስኬት የተሰማኝን ደስታ እገልጻለሁ ብለዋል። የእርሳቸው አመራር በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን ከድህነት ያወጣ፣ የዲጂታል ሕዝባዊ መሰረተ ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ያስፋፋ እና ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ የመሰረተ ልማት እድገትን በማምጣት ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ያስገኘ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በተከታታይነት ለደቡቡ የዓለም ክፍል (Global South) ጠንካራ ድምጽ በመሆን አገልግለዋል ሲሉም ገልጸዋል።
የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ይገኛል
Jun 9, 2026 1763
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ ከሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ክልሎች መካከል የ816 ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። ከዚህም መካከል የ24 የምርጫ ክልሎች ውጤቶች በቦርዱ ተረጋግጠው መጽደቃቸውም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በሰጡት መግለጫ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደው ልዩ ምርጫ መጠናቀቁንም ገልጸዋል። ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1ሺህ 139 ምርጫ ክልሎች ውስጥ ከሁለቱ ምርጫ ክልሎች በስተቀር በሁሉም የጊዜያዊ ውጤት መለጠፉን ገልጸዋል። በሀላባ አንድ እና በቀብሪ በያ ምርጫ ክልሎች ከምርጫ ጣቢያዎች ቦታ ርቀት የተነሳ የመደመር ስራ በምርጫ ክልል ደረጃ አለመጠናቀቁን ገልጸዋል። እስከ አሁን ባለው ሂደት የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤት በማዕከል ደረጃ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ሲሆን፤ የ24 ምርጫ ክልሎች ውጤት መጽደቁን አስታውቀዋል። የ501 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ላይ ከተካሄደው ውስጥ 353 በማዕከል ደረጃ መግባቱን ገልጸው፤ በክልል ምክር ቤት ከ638 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 463 ወደ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል።
በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎች ዛሬ ድምጻቸውን ሰጥተዋል - ምርጫ ቦርድ
Jun 9, 2026 1230
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች ለመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ድምጽ መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደውን ምርጫ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ቦርዱ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በመደበኛው ጠቅላላ ምርጫ በልዩ ሁኔታ ላልተሳተፉ ዜጎች የድምጽ መስጫ ቀን እንደሚያመቻች ገልጸዋል። ቦርዱ ለዚሁ የሚሆን ልዩ የምርጫ ጣቢያ በማዘጋጀት የተለያዩ ስራዎችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። ለአስፈጻሚዎች እና ለአስተባባሪዎች ስልጠና መስጠቱን ገልጸው፤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማድረጉንም ተናግረዋል። ምርጫውን ለማካሄድም በእነዚህ የምርጫ ጣቢያዎች በትላንትናው እለት የምርጫ ቁሳቁስ ሙሉ በሙሉ መቅረቡን ተናግረዋል። በካምፖች በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ሰዓትም በሁሉም ወታደራዊ ካምፖች እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ መጠለያዎች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሲካሄድ የቆየው ምርጫ ከአንድ ጣቢያ ውጪ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ገልጸው፤ በድምጽ አሰጣጥ ሂደቱም ያጋጠመ ችግር እንደሌለ ጠቁመዋል።
በአፋር ክልል በሚገኙ ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች ድምፃቸውን እየሰጡ ነው
Jun 9, 2026 978
ሰመራ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በሚገኙ ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች ድምፃቸውን እየሰጡ መሆኑን በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኀላፊ ጣሃ ዓሊ ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለያዩ ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ወይም በልዩ ሁኔታዎች በታቀደው መደበኛ የድምፅ መስጫ ቀን መሳተፍ ላልቻሉ ዜጎች የተራዘመ ወይም ልዩ የድምፅ መስጫ ቀን ያመቻቻል። ይህ አሠራር ማንኛውም ድምፅ የመስጠት መብት ያለው ዜጋ ከዴሞክራሲያዊ ሂደቱ እንዳይገለልና የምርጫው አካታችነት እንዲረጋገጥ ይረዳል። ቦርዱ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ልዩ የድምፅ መስጫ ቀናትን በማመቻቸት ዜጎች ድምጽ እንዲሰጡ ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህም መሰረት በሀገር ውስጥ በሚገኙ መጠለያዎችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም ዜጎች ድምፅ እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል።   በዚህ ጉዳይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኀላፊ ጣሃ ዓሊ እንደገለጹት፤ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ዛሬ ድምጽ እየተሰጠ ነው። መራጭ ዜጎችም ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በክልሉ ባሉ 19 ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምጽ እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። በዱብቲ፣ ገዋኔ፣ አሚባራና ገለአሎ ምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ አስራ ዘጠኝ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እየተካሄደ መሆኑንም አስታውቀዋል። በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎቹ የሚገኙ ዜጎችም ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም የሚፈልጉትን ፓርቲ በመምረጥ ላይ እንደሚገኙ አቶ ጣሃ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበር ጉዳይ ላይ አቋማችን የጸና ነው-የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jun 9, 2026 930
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበርና ሉዓላዊነቷን የማስጠበቅ ጉዳይ ላይ አቋማችን የጸና ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ታሪክ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም የተቃረኑ ባንዳዎች ሁሉ ከስመዋል፤አሁን ያሉትም የሚገጥማቸው ዕጣ ፈንታ ተመሳሳይ ይሆናል ብለዋል። የሀገርን ሉዓላዊነት ማስከበር፣የግዛት አንድነትን መጠበቅ እና የውስጥ ሰላምን ማስፈን እንደ ዋና ብሔራዊ ጥቅም የሚወሰድ መሆኑ ይታወቃል። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንኑ ለማስከበር እና ለማስጠበቅ በቁርጠኝነት እየሠራ ይገኛል። በአንድ ወቅት የባሕር በር የነበራት ኢትዮጵያ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የባሕር በር እንድታጣ የተደረገበት ሁኔታ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል። በዚህ ረገድ መንግሥት ጠንካራ የዲፕሎማሲ ጥረት እያደረገ ሲሆን ዜጎችም መሠረታዊ አጀንዳቸው አድርገውት ለምላሹ እየተሠራ መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ በተቃራኒ አንዳንዶች ከባዕዳን ጋር በመሰለፍ በባንዳነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን የሚጻረሩ እንዳሉ የሚታወቅ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ በኢትዮጵያ ታሪክ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በመቃረን የሚቆሙ ባንዳዎች መኖራቸውን አስታውሰዋል። እነዚህ አካላት የከሰሙ መሆኑን አንስተው፥ አሁን ያሉትም የሚገጥማቸው ዕጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊ እና የኢዜማ ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ታሪኩ ድንበሩ፤ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ለድርድር የሚቀርብ መሆን የለበትም ብለዋል። በመሆኑም ሁላችንም የሀገር ሰላምን በጋራ የመጠበቅ፣ የኢኮኖሚ ልማት ሥራዎችን በጋራ ማስቀጠል እና ከውጭ የሚቃጡ ጥቃቶችን በጋራ የመመከት ግዴታ አለብን ብለዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበርና ሉዓላዊነቷን የማስጠበቅ ጉዳይ ላይ የሁላችንም አቋማችን የጸና ነው ሲሉ ተናግረዋል። የነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ኡመር አብዱራህማን፤ የትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ የሚፎካከረው ከምንም በላይ ለሀገር እና ለሕዝብ ጥቅም ለመሥራት መሆን አለበት ብለዋል። ከዚህ በተቃራኒ በመቆም በሀገር ብሔራዊ ጥቅምና በዜጎች ደኅንነት ላይ መሥራት የባንዳነት ተግባር ስለመሆኑ ተናግረዋል። የሕዳሴ ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ሱራፌል እሸቱ፤ የትኛውም የፖለቲካ ተዋናይ ይሁን ዜጋ በብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ የተለየ አቋም መያዝ ተገቢነት የሌለው መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በመሆኑም የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ጨምሮ ሌሎችም ኢትዮጵያን በሚመለከቱ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ አቋማችን የጸና እና የማይናወጥ ነው ብለዋል።
የሀገራችንን ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን በመጠቀም ድምፃችንን ሰጥተናል-የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አባላት
Jun 9, 2026 912
ሰመራ፣ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ) የሀገራችንን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን፣ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን በመጠቀም ድምፃችንን ሰጥተናል ሲሉ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አባላት ገለፁ። በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ ማንኛውም መራጭ ድምፅ ለመስጠት በሚኖርበት ወይም በቋሚነት በሚሠራበት አካባቢ ተመዝግቦ መምረጥ እንዳለበት ይደነግጋል። ሆኖም ግን፣በተለያዩ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ምክንያቶች የተፈናቀሉ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች ውስጥ የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩበት ሁኔታ ይፈጠራል። ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን ያደራጃል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም በልዩ ሁኔታ ላይ ባሉ በሀገር ውስጥ መጠለያ ሊሚገኙና በመከላከያ ካምፖች ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ በመካሄድ ላይ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የሰሜን ምስራቅ ዕዙ አባላት እንዳሉት፥ ሰራዊቱ በታላቅ ጀግንነት የሀገሩን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር በማስከበር ላይ ይገኛል። ከዚህ ጎን ለጎን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ለሀገር ይበጃል ላሉት ፓርቲ ድምፃቸውን ሰጥተዋል።   አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል የሰሜን ምሰራቅ ዕዝ ኦዲት ኀላፊ ተወካይ ሻለቃ ንጋቱ ኩምሳ፤ ሰራዊቱ በላቀ ጀግንነት የሀገሩን ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን በዛሬው ዕለት በመምረጡ ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል። በቀጣይነትም በምርጫው ካሸናፊው ፓርቲ ጎን በመሆን የኢትዮጵያን ሰላም የማረጋገጥ፣ ዳር ድንበርን በቆራጥነት የማስከበር ሚናችንን እንወጣለን ብለዋል።   ሻለቃ ባሻ አባተ አርሲኖ በበኩላቸው፤ የተሰጠንን ሀገራዊ ግዳጅ ለመወጣትና የሀገራችንን ዳር ድንበር ለማስከበር የምንጊዜም ዝግጁነታቸውን ገልፀው፤ ከዚሁ ጎን ለጎን በምርጫው መሳተፍ በመቻላቸው እንዳስደሰታቸው ነው ያስረዱት። በምርጫው በመሳተፋቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው፤ ይህም ለሶስተኛ ጊዜያቸው መሆኑንም ተናግረዋል።   መቶ ዓለቃ ኢያሱ ጩማ፤ የሀገሬን ዳር ድንበር እያስከበርኩ በዚህ ወቅት ዴሞክራሲያዊ መብቴን ተጠቅሜ መምረጥ በመቻሌ ደስተኛ ነኝ ብለዋል።   7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በነፃነት መምረጥ መቻላቸውን የተናገሩት ደግሞ አስር ዓለቃ ታመነ ተሻለ ናቸው። የሀገሬን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር እየጠበቅኩና ሰላሟን እያስቀጠልኩ ከዚህ ጎን ለጎን መምረጥ በመቻሌ ደስ ብሎኛል ብለዋል።  
ማህበራዊ
አመራሩ ወቅቱን የዋጀ ዕውቀትን በመታጠቅ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ይጠበቅበታል
Jun 10, 2026 82
ደሴ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፡-አመራሩ ወቅቱን የዋጀ ዕውቀትን በመታጠቅና እንደ አስቻይ ሁኔታው በመምራት መሰረታዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚገባ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ አመለከቱ። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ አካዳሚክ ስታፍ ሰራተኞችና ለካውንስል አባላት ስልጠና እየሰጡ ነው።   አቶ ዛዲግ በስልጠናው ላይ እንዳሉት፤ አመራሩ ወቅቱን የዋጀ ዕውቀትን በመታጠቅ መሰረታዊ ለውጥ ማስመዝገብ ይጠበቅበታል ብለዋል። በተለመደውና ከዚህ ቀደም በነበሩ አሰራሮች መቀጠል ወቅቱ እንደማይፈቅድ ያስገነዘቡት አቶ ዛዲግ ከዘመኑ ጋር እኩል በመራመድና በመስራት በየዘርፉ ለውጥ ማምጣት አስፈላጊ ነው ያሉት። የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ አመራሩ የዓለምን ተለዋዋጭ ባህሪና ሁኔታ ተረድቶ በመምራት ውጤታማ መሆን እንዲችል ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በዚህም ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለአመራሩ፣ ለአካዳሚክ ስታፍ ሰራተኛውና ለካውንስል አባላት ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው በዚህም አቅምን በማጎልበት ውጤታማ ተግባር ማከናወን ይገባል ብለዋል።   እንዲሁም አውቆና ወቅቱን ተረድቶ በመስራት ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ከመፍጠር ባለፈ አቅላይ የፈጠራ ስራዎችን ማብዛት እንደሚገባም አመልክተዋል። ዩኒቨርሲቲው በተግባር ተኮር ትምህርት ብቁ ትውልድ ከመፍጠር ባለፈ ቴክኖሎጂ ላይ አተኩሮ በመስራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አክለዋል። ወቅቱን በዋጀ ክህሎትና እውቀት ተመርተን ውጤታማ ተግባር ለማስመዝገብ ስልጠናው ያግዘናል ያሉት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የዓለም አቀፍ ግንኘነትና አጋርነት ትብብር ዳይሬክተር አስረሴ ሞላ (ዶ/ር) ናቸው። ስልጠናውን በንቃት በመከታተል መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት እንደሚሰሩም ገልጸዋል። ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ላይም አመራሮች፣ የአካዳሚክ ስታፍ ሰራተኞች፣ የካውንስል አባላትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
በሆስፒታሉ ባገኘነው ነጻ የዓይን ቀዶ ሕክምና ብርሃናችን ተመልሷል
Jun 10, 2026 115
ደብረ ብርሃን፣ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-በደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ባገኙት ነጻ የዓይን ቀዶ ሕክምና ብርሃናቸው መመለሱን ታካሚዎች ተናገሩ። ሆስፒታሉ ከ1ሺህ 600 ለሚበልጡ ወገኖች ነጻ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ሕክምና አገልግሎት በዘመቻ እየሰጠ መሆኑን አስታውቋል።   ከሕክምና አገልግሎቱ ተጠቃሚዎች መካከል ከመንዝ ላሎ ወረዳ የመጡት ወይዘሮ አልማዝ ወርቁ ከአንድ ዓመት በላይ የዓይን ብርሃናቸውን አጥተው ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ተዳርገው ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት በሆስፒታሉ ባገኙት ነጻ የዓይን ቀዶ ሕክምና የዓይን ብርሃናቸውን በመመለሱ ችግራቸው መፈታቱን ተናግረዋል። በዓይን ሞራ ግርዶሽ ከሦስት ዓመት በላይ ለማየት ተቸግረው እንደነበረና ባገኙት ነፃ የዓይን ቀዶ ሕክምና መፍትሄ ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ የአንጎለላና ጠራ ወረዳ ነዋሪ አቶ ደበበ አበበ ናቸው። በዘመቻው የተደረገላቸው የዓይን ቀዶ ሕክምና ለአራት ዓመታት ከገጠማቸው የማየት ችግር እንደታደጋቸው የተናገሩት አቶ አበራ ላቀው የተባሉ ነዋሪ ደግሞ፣ በአሁኑ ወቅት የዓይን ብርሃናቸው በመመለሱ መደሰታቸውን ገልፀዋል። የዓይን ብርሃናቸውን ባጡበት ወቅት በሰዎች ድጋፍ ይንቀሳቀሱ እንደነበር አስታውሰው፣ ይህም በማህበራዊ እንቅስቃሴያቸው ላይ ተጽዕኖ አሳድሮ መቆየቱን ተናግረዋል። የሆስፒታሉ የዓይን ስፔሻሊስት ሀኪም ዶክተር ዓለማየሁ ባየ እንዳሉት፤ የዓይን ሞራ ግርዶሽ በወቅቱ መታከም ካልተቻለ ለዓይነስውርነት የሚዳርግ በሽታ ነው።   የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ በበኩላቸው፤ በግል ከፍለው መታከም ለማይችሉ የማህበረሰብ ክፍሎች ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ እና ተዛማጅ የሕክምና አገልግሎቶችን በነጻ እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። ከሰኔ 2 እስከ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው የሕክምና አገልግሎት ከ1 ሺህ 600 በላይ ሰዎችን ለማከም ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ እስካሁንም ለ231 ሰዎች የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ተችሏል ብለዋል።   ነጻ የሕክምና አገልግሎቱ በትብብር እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው፣ ሆስፒታሉ ባለፈው ህዳር ወርም 2018 ዓ.ም ከ2 ሺህ በላይ ለሆኑ ሰዎች መሰል የሕክምና አገልግሎት መሰጠቱን አስታውሰዋል።
በሲዳማ ክልል ለሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፈተናዎች ዝግጅት ተደርጓል
Jun 10, 2026 221
ሀዋሳ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ለሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፈተናዎች አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ በየነ በራሳ ገለጹ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ በራሳ የተደረገውን የቅድመ ዝግጅት በማስመልከት ከኢዜአ ጋር ቆይታ አደርገዋል። በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ 26 ሺህ 735 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና እንደሚወስዱ ገልጸዋል። በፈተናው የተማሪዎችን ውጤታማነት ለማሳደግ አስፈላጊ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን ገልጸው፤ የትምህርት ዓመቱ ከመጀመሩ ሁለት ወራት አስቀድሞ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የማዘጋጀት ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል። ዘንድሮ በክልሉ ከሚፈተኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል 50 ከመቶ የሚሆኑት ፈተናውን በበይነ መረብ እንደሚወስዱ ገልጸው፤ ለዚህም ኮምፒውተርን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችን የማሟላት ስራ ተከናውኗል ብለዋል። በተመሳሳይ የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችም ዘንድሮ በተለየ ሁኔታ በመፈተኛ ማዕከላት ፈተናውን እንደሚወስዱ ጠቁመው፤ ይህም ኩረጃን ለመከላከል እና ምቹ የፈተና አስተዳደር ሥርዓት እንዲኖር ያግዛል ብለዋል። በሦስቱም የትምህርት እርከኖች የሚፈተኑ የክልሉ ተማሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ከመደበኛ የትምህርት ሰዓት ውጪ የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲወስዱ መደረጉን ተናግረዋል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ተማሪዎችን በተለያየ መንገድ በመደገፍ ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ግብ ተይዞ ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል። የሃዋሳ አዲስ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ትእዛዙ ባንዳው፤ በትምህርት ቤቱ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚወስዱ ከ420 በላይ ተማሪዎችን ለፈተና ሲያዘጋጁ መቆየታቸውን ገልጸዋል። መምህራን በማጠናከሪያ ትምህርት ተፈታኝ ተማሪዎችን የማብቃት ሥራ ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፤ ሞዴል ፈተናዎችን በመስጠት ፈተናን የማለማመድ ሥራ መሰራቱንም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅተም ተማሪዎችን በበይነ መረብ ለማስፈተን የሚያስችሉ ዝግጅቶችን ከማድረግ ጎን ለጎን ተፈታኞችን በስነ ልቦና የማዘጋጀት ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከሃዋሳ አዲስ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ሃሚዲ የሱፍ እና አዲስ ላቀው፤ በግላቸው ባደረጉት ጥረትና በትምህርት ቤቱ ድጋፍ ለፈተናው መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የማጠናከሪያ ትምህርት፣ ሞዴል ፈተናዎችንና በበይነ መረብ ፈተና መውሰድ የሚያስችላቸውን የቴክኖሎጂ ድጋፍ ማግኘታቸውን ገልጸው፤ በፈተናው የተሻለ ውጤት ለማምጣት መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል።
በብሔረሰብ አስተዳደሩ ከ197 ሺህ በላይ ወጣቶች በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ይሳተፋሉ
Jun 10, 2026 203
ሰቆጣ ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ከ197 ሺህ በላይ ወጣቶች በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንደሚሳተፉ የብሔረሰብ አስተዳደሩ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የዜጎች በጎ ፈቃድ አገልግሎትና የወጣቶች ንቅናቄ ተሳትፎ ቡድን መሪ አቶ ሙሉጌታ ስኳር ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ማህበራዊ ችግሮች በመፍታት ረገድ ውጤት እየተመዘገበበት ነው። የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠልም በመጪው ክረምት 197 ሺህ 250 ወጣቶችን በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በማሳተፍ 584 ሺህ 860 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል። በአገልግሎቱም 518 የአቅመ ደካማ ቤቶችን በአዲስ የመገንባትና የመጠገን፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ ምርታማነትን የማሳደግ፣ የትምህርት፣ የጤናና ሌሎች 17 ተግባራት ላይ እንደሚከናወን ገልፀዋል። ከሰኔ 15/2018 ዓ/ም ጀምሮ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚሳተፉ ወጣቶችን የመመዝገብ፣ የመለየትና የማዘጋጀት ስራ በማከናወን ከሃምሌ ጀምሮ ተግባሩ እንደሚጀመር አስረድተዋል። የቅድመ ዝግጅት ስራውን ለማከናወንም ኮሚቴ ተዋቅሮ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው ወጣቶች ከወዲሁ ተመዝግበው ዝግጅት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።   በአማራ ወጣቶች ማህበር የዋግ ኽምራ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ወጣት ወንድሙ ገብረ እግዚአብሄር ወጣቶች የክረምቱን የእረፍት ጊዜ በበጎ ተግባር ላይ እንዲያሳልፉ እየተሰራ ነው ብሏል። በብሔረሰብ አስተዳደሩ ባለፈው ዓመት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት 377 ሺህ 360 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ኢኮኖሚ
የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የታክስ አሰራርን በማዘመን ፍትሐዊነትና የሕግ ተገዢነትን ለማረጋገጥ እገዛ ያደርጋል
Jun 10, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡- የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የታክስ አሰራርን በማዘመን ፍትሐዊነትና የሕግ ተገዢነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የአስረጂ መድረክ ተካሂዷል።   የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቃዱ ሆረታ በዚህ ወቅት፤ የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ከኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ጋር የተጣጣመ ዘመናዊ የታክስ አሰራር ለመፍጠር ያስቻላል ብለዋል። በታክስ ከፋዩ ማህበረሰቡ የሚነሱ መሰረታዊ የፍትሐዊና የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችንም መፍትሔ ለመስጠት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል። የመንግሥትን ገቢ የመሰብሰብ አቅም በማጎልበት ተጠያቂነትን ከግልጸኝነት ያጣመረ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት እንደሚያስችልም ተናግረዋል። የምክር ቤቱ አባላትና የሕግ ማዕከል ባለሙያዎችም፤ በማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ የታክስ ስሌት፣ የይርጋ ጊዜ ገደብ፣ የታክስ ከፋይ መስተንግዶና ተያያዥ ጉዳዮችን በማስመልከት ጥያቄ አንስተዋል። በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሕግ አማካሪ ዋሲሁን አባተ፤ በረቂቅ አዋጁ የይርጋ ጊዜው አስር ዓመት ሆኖ መቀመጡ በታክስ ከፋዩ ላይ የሚኖረውን ጫና መቀነስ እንደሚያስችል ተናግረዋል። በገንዘብ ሚኒስቴር የሕግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፈ ተወዳጅ መሐመድ፤ የታክስ ደረሰኝ አለመስጠት ተመሳሳይ የገንዘብ ቅጣት መጣሉ ሆን ተብሎ የሚፈጸምን የታክስ ማጭበርበር በማስቀረትና ደረሰኝ መቁረጥን ባህል ያደርጋል ብለዋል። በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ አማካሪ ያሬድ ፍቃደ በበኩላቸው፤ የገለልተኛ አስማሚ ስርዓት ገለልተኛ ሆኖ የሚቋቋም በመሆኑ ግብር ከፋዩ የሚገጥመውን ችግር መፍቻ ተጨማሪ አማራጭ ነው ብለዋል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጀ፤ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ኢኮኖሚው በሚያመነጨው ልክ ገቢን ለመሰብሰብና የታክስ አስተዳደርን ለማዘመን እንደሚያስችል ተናግረዋል። በአስረጂ መድረኩ ግልፅ ያልሆኑ ጉዳዮች ይበልጥ ማጥራት የሚያስችል ማብራሪያ መሰጠቱን ጠቁመው የተደረጉት ማሻሻያዎች ፍትሐዊነትንና የሕግ ተገዢነትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።  
የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝነትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ የፀሃይ ሃይል ልማትን ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቷል
Jun 10, 2026 198
አዳማ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝነትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ የፀሃይ ሃይል ልማትን ለማስፋፋት ትኩረት መሰጠቱን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለፀ። ሚኒስቴሩ አማራጭ የኃይል ምንጮችን ለማስፋፋትና በዘርፉ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎን ለማጠናከር ያለመ የውይይት መድረክ በአዳማ በማካሄድ ላይ ይገኛል ። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንደገለፁት ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም በታዳሽ ሃይል ልማት ላይ በትኩረት እየሰራች ትገኛለች። በተለይ በውሃ፣ በፀሃይ፣ በንፋስና በጂኦተርማል ሃይል ልማት ላይ ትኩረት መደረጉን ገልጸው በአሁኑ ወቅት 96 በመቶ የሚሆነው የሃይል አቅርቦት ከኃይድሮ ኤሌክትሪክ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ አስተማማኝና ዘላቂ የሃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥ አማራጭ የሃይል ልማት የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። ከአማራጭ ታዳሽ ሃይል ልማት የፀሃይ ሃይል ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው ልማቱ ላይ የግሉን ዘርፍና ባለድርሻ አካላትን ለማሳተፍ የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎችና አሰራሮች መዘርጋታቸውን ገልጸዋል። በተለይም የፀሀይ ኃይል ልማቱ አርሶና አርብቶ አደሮች በመስኖና በተለያዩ የስራ መስኮች በዘላቂነት እንዲሳተፉና ህይወታቸው እንዲለወጥ በማድረግ ረገድ ቁልፍና አጋዥ መሆኑንም ተናግረዋል። ከዋና የሃይል መስመር ርቀው የሚገኙ ወረዳዎችና የገጠር ቀበሌዎችን የመብራት ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ንፁህ የመጠጥ ውሃ እንዲያገኙ ብሎም በመስኖ ልማት እንዲሳተፉ ጭምር ውጤት እየተገኘበት ነው ብለዋል።   በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የዩ.ኤን.ዲ.ፒ አፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮግራም ማኔጀር አቶ ይመስላል ተፈራ በበኩላቸው የግሉ ዘርፍ በፀሃይ ሃይል ልማት እንዲሳተፍና ዘርፉ በትብብር እንዲለማ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል። በተለይ ከህግ ማዕቀፎች ጀምሮ በርካታ የአሰራር ማሻሻያዎች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው የሃይል ዘርፉ አንዱ የኢንቨስትመንት መስክ መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይ በግብርና ዘርፍ ብቻ የተወሰኑ የህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች በጸሃይ ኃይል ልማት በመሳተፍ ገበያ ተኮርና የገቢ አቅማቸውን የሚያሳድግ ሰፋፊ የግብርና መስኖ ልማት እንዲያከናውኑ ዕድልን የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በዚህም ፕሮግራሙ ለህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች በጸሃይ ኃይል ልማት ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ከመስጠት ባለፈ በፓይለት ደረጃ በሐዋሳ፣ ሶማሌና ቄለም ወለጋ ዞኖች እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።   በኦሮሚያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ የኢነርጂ አቅርቦት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሶሬሳ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በታዳሽ ሃይል ልማት ማስፋፋት ላይ በትኩረት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። በተለይ በቄለም ወለጋ ላሎ ቂሌ ወረዳ የሚኒግሪድ የፀሃይ ሃይል ልማት ለማከናወን በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልጸው በተጨማሪም የክልሉ የህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች በፀሃይ ኃይል ልማት እንዲሳተፉ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።
የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው
Jun 10, 2026 275
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ ገለጹ። በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በ21 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የመስኖ ስንዴ ሰብል ስብሰባ ተጀምሯል።   በዚሁ ጊዜ ምከትል ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት የበጋ መስኖ ሰብል ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እያገዘ ይገኛል። በኦሮሚያ ክልል እየተከናወነ የሚገኘው የበጋ መስኖ ልማት ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም የአርሶ አደሩን ገቢ በዕጥፍ እያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል። የልማት ስራው ግብርናውን ለማሸጋገር ጭምር እያገዘ መሆኑን ጠቅሰው የግብርና ሜካናይዜሽን ግብዓቶችን በብዛት፣ በጥራት እንዲሁም ፈጠራን መጠቀም እያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ኢኒሼቲቭ መልክ እየተካሄደ ሲሆን ይህም በክረምት ዝናብ ብቻ ተወስኖ የነበረው የግብርና ባህል መለወጥ እያስቻለ ነው ብለዋል።   በዚህ ወቅት የክልሉ አርሶ አደር በሁሉም የልማት ወቅቶች የግብርና ስራን እያከናወነ ሲሆን የገጠር ልማትን ከመሠረቱ ለመቀየር የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ነው ያሉት። አቶ አወሉ አብዲ አክለውም በዞኑ በትራክተር ማረስና በኮምባይነር ሰብል የመሰብሰብ ባህል እየተለመደ መጥቷል ብለዋል።
በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል
Jun 10, 2026 191
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ እስታወቀ። የጋምቤላ ክልል ሰፊ ለም መሬት፣ ከፍተኛ የውሃ አማራጭ እና ለተለያዩ ሰብሎች ተስማሚ የሆነ የአየር ንብረት ያለው በመሆኑ ለግብርና ኢንቨስትመንትም ሆነ በአነስተኛ እርሻ ላይ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች ትልቅ አቅም ያለው ነው። በመሆኑም ክልሉ ያለውን ፀጋ በመጠቀም የክልሉን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና ክልሉ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ መጫወት የሚገባውን ሚና እንዲወጣ በርካታ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆኑ ተገልጿል። የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አንድሮው ቱት ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ በተያዘው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው መሬት አንድም ማሳ ጦም እንዳያድር በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች የተጠናከረ የንቅናቄ ስራ እየተከናወነ ነው። በእስካሁኑ ሂደትም በምርት ዘመኑ ለማልማት ከታቀደው 180 ሺህ ሄክታር መሬት ውስጥ 130 ሺህ ሄክታሩ በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን ጠቁመው ይህም የእቅዱን 72 ከመቶ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ ሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች ቀድመው ለሚዘሩ የበቀሎ፣ የሰሊጥ፣ የለውዝና ሌሎች የሰብልና የጓሮ አትክልት የተዘጋጁ ማሳዎች በዘር መሸፈናቸውን ገልጸዋል። በተለይም የበልግ ዝናብን የሚጋሩት በማጃንግ ዞን የሚገኙ የጎደሬና የመንጌሽ ወረዳዎች ያለውን ምቹ ስነ-ምህዳር በመጠቀም ኩታ ገጠምን ጨምሮ የመኸር ግብርና ልማት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። ቀሪውን ማሳ ዘግይተው በሚዘሩ ሰብሎች ለማሸፈንም የባለሙያዎች ስምሪት በማካሄድ የግብዓት አቅርቦትን ጨምሮ የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አክለዋል። በምርት ዘመኑ እየለማ ያለው መሬት ከቀዳሚው ዓመት በስምንት ሺህ ሄክታር ብልጫ ያለው መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህም ከ5 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ግብ መጣሉን አቶ አንድሮው ገልጸዋል። በጎደሬ ወረዳ ጎሽኔ ቀበሌ በኩታ ገጠም ልማት የተሰማሩት አርሶ አደር አብረሃም አባተ ከመጋቢት ወር አጋማሽ ጀምሮ የበቆሎ ሰብል በኩታ ገጠም ማልማታቸውንና ሰብሉም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የግብርና ልማት በኩታ ገጠም ሲሰራ የግብርና ግብዓቶችን ለማግኘትና በሰብል ላይ ጉዳት የሚያደርሱ እንስሳትን ለመከላከል ጭምር የጎላ ጠቀሚታ እንዳለው የገለጹት ደግሞ የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ኢቲባ ድንገታ ናቸው። በዘንድሮው የመኸር እርሻ በኩታ ገጠም ማልማት በመጀመራቸው ምርጥ ዘርና ሌሎች ግብዓቶችን በወቅቱ ማግኘት እንዳስቻላቸውም ተናግረዋል በክልሉ ማጃንግ ዞን በሚገኙ የጎደሬና መንጌሽ ወረዳዎች በኩታ ገጠም የለማ የበቆሎ ሰብል በዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች ተጎብኝቷል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤና የቴክኖሎጂ ውድድር ከፊታችን አርብ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Jun 10, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤና የቴክኖሎጂ ውድድር ከመጪው አርብ ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያካሂደውን ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ እና የቴክኖሎጂ ውድድር በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።   የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ሙሉጌታ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ኢንስቲትዩቱ በምርምርና በቴክኖሎጂ ልማት ረገድ በርካታ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ይህ ዓለም አቀፋዊ የምርምር ጉባዔ እና የቴክኖሎጂ ውድድርም፤ ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ የጀመራቸውን የፈጠራና የምርምር ስራዎች ይበልጥ አጠናክሮ እንዲቀጥል ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን ይህንን ጉባኤ በስኬት ለማካሄድ ተቋሙ በቂ ዝግጅት ማድረጉንም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። ዓለም አቀፋዊ የምርምር ጉባዔ እና የቴክኖሎጂ ውድድርም ከሰኔ 5 እስከ 7 2018 ዓ.ም የሚቆይ እንደሚሆን አመልክተዋል፡፡ በጉባኤው ከ 16 አገራት የተወጣጡ ተመራማሪዎች እና ሌሎች አካላት የሚሳተፉ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከላት ከ230 ሺህ በላይ ተገልጋዮችን ማስተናገድ ችለዋል
Jun 10, 2026 236
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ስራ ከጀመረበት አጭር ጊዜ ጀምሮ ከ230 ሺህ በላይ ህዝብን ማስተናገዱን የከንቲባ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ማዕከላቱ 99 በመቶ የተገልጋዮች እርካታን ማስመገባቸውንም አስታውቋል። የአዲስ አበባ ከተማን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመንና ለአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የተወጠነው ይህ አዲስ መሶብ ፕሮጀክት ታላቅ ስኬት እያስመዘገበ እንደሚገኝ አመልክቷል።   እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 11 ማዕከላትን ለመክፈት ታቅዶ እየተሰራ ሲሆን፣ እስከ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ዘጠኙ ማለትም አራዳ፣ ቦሌ፣ ልደታ፣ ቂርቆስ፣ አዲስ ከተማ፣ ጉለሌ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ፣ ኮልፌ ቀራኒዮ እና የካ ሙሉ በሙሉ ወደ አገልግሎት ማስገባት ተችሏል። የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ደሳለኝ ተረፈ (ኢ/ር) እንደገለጹት፣ ቀሪዎቹ የአቃቂ እና የለሚ ኩራ ማዕከላት የግንባታ አፈጻጸማቸው ከ99 ነጥብ 5 በመቶ በላይ በመሆኑ በቀጣይ ቀናት ተመርቀው አገልግሎት መጀመር የሚያስችላቸው ዝግጅት ተጠናቅቋል።   ማዕከላቱ ስራ ከጀመሩበት አጭር ጊዜ ጀምሮ ከ230 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ያስተናገዱ ሲሆን፣ በተደረገው ዳሰሳም የተገልጋዮች እርካታ 99 በመቶ መድረስ መቻሉን ገልጸዋል። ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በከተማ አስተዳደሩ ልዩ ድጋፍ የባለሙያ ቅጥር፣ ስልጠና እና መሰረታዊ ግብዓቶች ቀድመው በመሟላታቸው መሆኑንም ጨምረው ጠቅሰዋል።
የዲጂታል ፋይናንስና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀልን ለመከላከል ከፍትህና የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው
Jun 10, 2026 204
አዳማ ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦የዲጂታል ፋይናንስና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀልን ለመከላከል ከፍትህና የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ኢትዮ - ቴሌኮም አስታወቀ። "የኢትዮ ቴሌኮም እና የፍትህ ተቋማት ጥምረት ለዲጂታል ኢትዮጵያ ደህንነት" በሚል መሪ ሀሳብ በዲጂታል ፋይናንስና የቴሌኮም ማጭበርበር እንዲሁም መሰረተ ልማት ላይ እየደረሰ ባለው ጉዳትና መፍትሄዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሊጋል ኦፊሰር አቶ ለማ ተሰማ፤ በቴሌኮም ዘርፍ የተገኘውን ስኬት ለማስቀጠል ኩባንያው የተለያዩ ስትራቴጂዎችን በመንደፍ ለተግባራዊነቱ እየተጋ ይገኛል ብለዋል።። ባለፉት ዓመታት ተግባራዊ የሆኑት የቴሌኮም እና የዲጂታል አገልግሎቶች አካታች ሀገራዊ ልማትን በማፋጠን ረገድ ወሳኝ ሚና መጫወታቸውን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን ቀጣይ መዳረሻ እና ዲጂታል መፃዒ ዕድል የተሳካ ለማድረግ የሶስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ በመቅረጽ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል። አዲሱ ስትራቴጂ “አድማስ ዲጂታል” ኢትዮ ቴሌኮምን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እና በዲጂታል የጎለበተ ኩባንያ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸው ሀገራዊ የልማት አጀንዳዎችን በማፋጠን፣ በቀጣናውና በዓለም አቀፍ የዲጂታል ኢኮኖሚ አዳዲስ ዕድሎችን ለመክፈት ወሳኝ መሆኑንም አስረድተዋል። በኩባንያው ያለፉት አመታት ስኬታማ ግስጋሴ ውስጥ የተለያዩ ተግዳሮቶች አጋጥመዋል ያሉት አቶ ለማ፤ በተለይም የዲጂታል ፋይናንስ እና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀሎችን ጠቅሰዋል። በቴሌኮም መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀም ዘረፋና ስርቆትም ሌላኛው ችግር መሆኑን አንስተው እነዚህን ወንጀሎች ለመከላከል በተለይም ከፍትህ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።   በኢትዮ ቴሌኮም የሕግ ጉዳዮች አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ወርቁ ታየ፤ የስልጠና መድረኩ ያተኮረው በዲጂታል ፋይናንስ ላይ የሚፈጸም ወንጀል፣ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል እንዲሁም የቴሌኮም መሠረተ ልማት ላይ የሚፈፀም ወንጀልን ለመከላከል ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። በሀገሪቷ የዲጂታል ፋይናንስና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀልን ለመከላከል ከፍትህና የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በመድረኩ ከፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ፣ ከፖሊስና ፍርድ ቤቶች የተውጣጡ የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ተቋሙ አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና ምቹ የሚያደርጉ በርካታ የዲጂታላይዜሽን ስራዎችን እያከናወነ ነው
Jun 10, 2026 348
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሰራሩን ዘመናዊ ከማድረግ ባለፈ የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና ምቹ የሚያደርጉ በርካታ የዲጂታላይዜሽን ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡ ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን በበይነ-መረብ ለተፈታኞች ማድረስ የሚያስችል አቅም መፈጠሩንም አመልክተዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ይፋ የተደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በሀገሪቱ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ላይ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎ በቅርቡ ይፋ ሆኖ በትግበራ ላይ የሚገኘው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂም ሀገሪቱን በዲጂታል ዘርፍ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ሰፊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል ግንባታ ዘርፍ እያከናወነችው ባለው ተግባር ዘርፈ-ብዙ ስኬቶች እየተመዘገቡበት ነው፡፡ ኢትዮጵያ በምታደርገው በዚህ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ተቋማቸው የራሱን ሚና ለመጫወት አሰራሩን በቴክኖሎጂ የመቃኘት ሰፊ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህም ተቋሙ የሚሰጣቸውን ልዩ ልዩ አገልግሎቶች ዘመኑን የዋጁ ለማድረግ እየተቻለ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትግበራ ወቅት የተለያዩ ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን በአብዛኛው በበይነ-መረብ ለተፈታኞች ማድረስ የሚያስችል አቅም መፈጠሩን አመልክተዋል። ከተፈታኞች ባሻገር ሌሎች አገልግሎት ፈላጊዎችም ከተቋሙ ድረ-ገጽና የበይነ-መረብ መተግበሪያዎች ጋር ተያያዥ የሆኑ ምቹ አሰራሮች መዘርጋታቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ዜጎች በአካል ወደ ተቋሙ መምጣት ሳይጠበቅባቸው ባሉበት ቦታ ሆነው፤ የጠፋባቸውን ወይም የተበላሹባቸውን የትምህርት ማስረጃዎች ማመልከትና ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ ማግኘት የሚችሉበት አሰራር መፈጠሩን አብራርተዋል። በተጨማሪም የትምህርት ማስረጃ ማጣራት ጥያቄዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መንገድ ምላሽ እንዲያገኙ መደረጉን ገልጸዋል። ተቋሙ በቀጣይም ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር አብሮ ለመራመድና ለዜጎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ቴክኖሎጂን የማላመድና አቅምን የማሳደግ ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። ይህም ማህበረሰቡ ከዲጂታላይዜሽን ተጠቃሚ እንዲሆንና የተቋሙ አገልግሎት ተደራሽነት ይበልጥ እንዲሰፋ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት አመልክተዋል።
ስፖርት
አበረታች ቅመሞች የመጠቀም ወንጀልን ለመከላከል የፍትህ አካላት ቅንጅታዊ አስተዋጾ ወሳኝ ነው
Jun 10, 2026 93
አዳማ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ አበረታች ቅመሞች የመጠቀም ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የፍትህ አካላት አስተዋጾ ወሳኝ መሆኑን የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ ከፌዴራል ፖሊስ እና ከፍትህ አካላት ጋር ወንጀሉን በቅንጅት የመከላከል ሥራውን ውጤታማ ለማድረግ ያለመ የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል።   የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን ይደርሳል በወቅቱ እንደገለጹት፤ የተቀናጀ የፀረ-አበረታች ቅመሞች መከላከልና መቆጣጠር ሥራ የዜጎችን ሁለንተናዊ ደህንነት ለመጠበቅ የሚደረገው ጥረት አንዱ አካል ነው። አበረታች ቅመሞችን መጠቀም በህግ የተከለከለ የወንጀል ተግባር በመሆኑ፣ ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የፍትህ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን አመልክተዋል። የውይይት መድረኩም የፀጥታና የፍትህ አካላት ከባለስልጣኑ ጋር በቅንጅትና በትብብር እንዲሰሩ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል። "ድርጊቱ የአትሌቲክስ ዘርፉን ከመጉዳት ባለፈ በሀገር ገፅታ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድር በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር መስራት አስፈልጓል" ብለዋል። ባለፉት ዓመታት የህግ ማዕቀፎችን ከማውጣትና የባለድርሻ አካላትን ትብብር ከማጠናከር አንጻር አመርቂ ሥራዎች እንደተሰሩ የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ይህን ለማስቀጠል ቅንጅታዊ ሥራን ይበልጥ ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ድርጊቱ በስፖርተኞች ላይ የስነ-ልቦና ጫና ከመፍጠር ባለፈ የተወዳዳሪነት አቅምን የሚፈታተን ወንጀል በመሆኑ መከላከሉና መቆጣጠሩ የጋራ ሃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት የባለስልጣኑ የውጤት አስተዳደርና ህግ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ንጋቱ መኮንን እንዳሉት፤ አበረታች ቅመሞችን የመጠቀም የህግ ጥሰቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መጥተዋል። እስካሁን እየተወሰዱ ያሉ የህግ እርምጃዎች በሚፈለገው ደረጃ ባለመሆናቸው ችግሩን ከመፍታት አኳያ ክፍተቶች እንደነበሩ አስታውሰዋል። ችግሩን ለመፍታት የፀረ-አበረታች ቅመሞች ህግ ማዕቀፎች በተግባር ላይ ውለው ውጤታማ እንዲሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተቀናጀ መልኩ መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የስፖርት ዲፕሎማሲን ማስተዋወቅ ያለመ የዲፕሎማቶች የእግር ኳስ ውድድር በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Jun 10, 2026 154
አዲስ አበባ፤ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦ አራተኛው የዲፕሎማቶች የእግር ኳስ ውድድር ቅዳሜ ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ይከናወናል። ውድድሩን ያዘጋጁት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከዩናይትድ ኪንግደም፣ካናዳ እና ሜክሲኮ ኤምባሲዎች ጋር በመተባበር ነው። የፌዴሬሽኑ እና የኤምባሲዎቹ ተወካዮች ስለ ውድድሩ አላማ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ። በውድድሩ ላይ ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ ከ30 በላይ ኤምባሲዎች፣ የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና አጋሮች ይሳተፋሉ። ውድድሩ የስፖርት ዲፕሎማሲ ለማስተዋወቅ፣ ዓለም አቀፍ ግንኙነት እና የባህል ልውውጥን ማጠናከር ዓላማ መሆኑ ተመላክቷል። ውድድሩ ቅዳሜ ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚካሄዱ ሲሆን፥ በዕለቱም የተለያዩ ዓለም አቀፍ ኤምባሲዎችንና ድርጅቶችን የወከሉ 25 የእግር ኳስ ቡድኖች ይወዳደራሉ። በውድድሩ ላይ ከ2 ሺህ 500 በላይ ታዳሚዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከእግር ኳስ ውድድሩ በተጨማሪ የተለያዩ ሁነቶች እንደሚካሄዱ ተመላክቷል። ውድድሩን በመጠቀም የዲፕሎማሲ፣ የንግድ እና የፖለቲካ አጋርነቶችን ለማጠናከር ታልሟል። ውድድሩ የአዲስ አበባን የዓለም አቀፍ ግንኙነት ወሳኝ ማዕከልነቷን ይበልጥ እንደሚያጎላ በመግለጫው ላይ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ለውድድሩ ዝግጅት ድጋፍ እንዳደረጉም ተመላክቷል።
አካባቢ ጥበቃ
በክልሉ ከብክለት የፀዳ ከባቢን በመፍጠር ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራት እየተደረገ ያለው ጥረት ይጠናከራል
Jun 10, 2026 147
ሆሳዕና ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ) ፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከብክለት የፀዳ ከባቢን በመፍጠር ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራት እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ገለፀ። ቢሮው "ብክለትን እንቀንስ፣ እንከላከል" በሚል መሪ ሐሳብ ከአምራች ኢንዱስትሪዎች፣ ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በህግ ተከባሪነት ዙሪያ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል።   የቢሮው ኃላፊ አቶ አብርሃም መጫ በወቅቱ እንዳሉት፤ በክልሉ ከብክለት የፀዳ ከባቢን በመፍጠር ጤናማና አምራች ዜጋን ለማፍራት እየተደረገ ያለው ጥረት ይጠናከራል። ለዚህም ከኢንዱስትሪዎች የሚወገዱ ቆሻሻዎችን በአግባቡ የማስወገድ ስራ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ጠቁመው ይህንንም ለማጠናከር የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። በክልሉ የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚን ለመንገባት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርና የፅዱ ኢትዮጵያ ኢንሼቲቮች ትግበራ መከናወኑን ጠቅሰዋል። በተለይም ከብክለት የጸዳ አካባቢን ለመፍጠር በተደረጉ ጥረቶች እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶችን ለማስፋት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባም አሳስበዋል።   ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል በሆሳዕና ከተማ የምስጋና ዱቄት ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ደመቀ በበኩላቸው ፋብሪካው ተረፈ ምርቶችን በአግባቡ በማስወገድ አካባቢውን ከብክለት ለመጠበቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለስኬቱም የተረፈ ምርት ማስወገጃን የማዘጋጀትና ምድረ ግቢውን በአረንጓዴ ልማት የመሸፈን ተግባር መከናወኑን አስረድተዋል። ፋብሪካው በጤና ባለሙያዎች ድጋፍና ክትትል ከብክለት የፀዳ አካባቢን ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በወራቤ ከተማ የአበሩስ ዱቄት ፋብሪካ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ነስሬ ናቸው።   ፋብሪካው ለፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ሴፍቲ ታንክን በመጠቀም ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት መስጠቱን ጠቁመዋል። በቀጣይም ፋብሪካው ንፅህናው የተጠበቀ ምርትን ለማህበረሰቡ ተደራሽ የማድረግ ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ የክልል ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሀገር በቀል የአካባቢ ጥበቃ ባህልን በማጠናከር ተፈጥሮን የመንከባከብ ሥራ እየተከናወነ ነው
Jun 10, 2026 177
ዲላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሀገር በቀል የአካባቢ ጥበቃ ባህልን በማጠናከር ተፈጥሮን የመንከባከብ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ የአካባቢ ጥበቃና የአየር ለውጥ ባለስልጣን ገለጸ። በክልሉ ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ቀን "ለአየር ንብረት ለውጥ ተግባራዊ እርምጃ" በሚል መሪ ሀሳብ በአከባቢ ጽዳት፣ በችግኝ ተከላ እና በፓናል ውይይት በዲላ ከተማ ተከብሯል። ቀኑ ስለአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ ከመፍጠር ባለፈ ተግባራዊ እርምጃ ማጠናከርን ዓላማ ያደረገ መሆኑ ተመላክቷል። የ‎ባለስልጣኑ ሃላፊ ግዛቴ ግጄ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ የሚያስከትለውን አደጋ ለመቀነስ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ጥረት እየተደረገ ነው። በተለይ በጌዴኦ፣ ኮንሶ፣ የኦሞ ሸለቆዎችና መሰል የክልሉ አካባቢዎች በሀገር በቀል የአካባቢ ጥበቃ ባህል ዓለም አቀፍ እውቅና እንዳላቸው አንስተው ይህንን በማጠናከር ተፈጥሮን የመንከባከብ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም በአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ አልፎም የታዳሽ ሃይል አጠቃቀምን በማሻሻል ብክለትን በመቀነሱ በኩል ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። ‎የአካባቢ ጥበቃ የጋራና የተቀናጀ ተግባራዊ ምላሽ ይፈልጋል ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ናቸው። ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ተከላ በማከናወን ዞኑ የሚታወቅበትን ሀገር በቀል የአካባቢ ጥበቃ እውቀት ከማጠናከር ባለፈ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል። ‎የዲላ ከተማ ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው ከአየር ንብረት ተጽዕኖ ነጻ የሆነች ከተማ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። በከተማው የተከናወኑ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት እንዲሁም የችግኝ ተከላና የጽዳት ስራዎች ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ መቀነስ የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል
Jun 8, 2026 979
ባህር ዳር፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን የክልሉ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። ዓለም አካባቢ ቀን "የአየር ንብረት ለውጥ ተጽኖን መታደግ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል።   የባለስልጣኑ ዋና ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ በመድረኩ እንደገለጹት፣ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያገዘ ነው። የኮሪደር ልማትም ከተሞችን ጽዱ፣ ውብና አረንጓዴ በማድረግ የአካባቢ ጥበቃንና እንክብካቤ ሥራ እንዲፋጠን አስተዋጾ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። ማንኛውም የልማት ፕሮጀክት ዘላቂነቱ የሚረጋገጠው ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በተጣጣመ መልኩ ሲተገበር መሆኑን ገልጸው፣ ይህም በክልሉ ተግባራዊ መደረጉን ጠቁመዋል። በክልሉ የልማት ሥራዎች ከአየር ንብረት ጋር ተጣጥመው እንዲከናወኑ መደረጉ እንደ ጎርፍ እና በረሀማነት ያሉ ችግሮችን ለመቀነስ መቻሉን ተናግረዋል። በአማራጭ የሃይል አቅርቦት ላይ የተመሰረተ ልማትም የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን አስረድተዋል። የአካባቢ ብክለትን ለመከላከልም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለህብረተሰቡ በዘመናዊ ቆሻሻ አወጋገድ ላይ ትምህርት በመስጠት ለውጥ እየታየ መምጣቱን ጠቁመዋል። ይህም ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በባለስልጣኑ የአየር ንብረት ለውጥ አካቶ ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አወቀ ይታይ የመወያያ ጽሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በግብርና፣ በትራንስፖርትና በከተማ ልማት ዘርፎች የአየር ንብረት ጉዳይን አካቶ እየተሰራ ነው።   በማሳያነትም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና በኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።
በክልሉ በሚቀጥሉት የክረምት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለመኸር እርሻ አመች ነው
Jun 8, 2026 655
ጋምቤላ፤ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በሚቀጥሉት የክረምት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለመኸር እርሻው አመች መሆኑን በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋምቤላ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ለ2018 ዓ.ም የክረምት ወቅት ያወጣው ትንበያ እንደሚያሳየው፣ በዘንድሮው መኸር የሚኖረው የዝናብ ስርጭት መደበኛና ለአዝመራው አመቺ እንደሚሆን ይጠበቃል። ይህ መረጃ ክልሉ ካለው ሰፊ የሩዝ፣ የበቆሎና የጥራጥሬ ሰብሎች ልማት አቅም አንጻር አርሶ አደሩና የኢንቨስትመንት አካላት አስቀድመው እንዲዘጋጁ ትልቅ እገዛ ያደርጋል። የጋምቤላ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋሁን ዓለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በሚቀጥሉት የክረምት ወራት የሚኖረው ዝናብ መደበኛና ብዙ ከመደበኛ ያላለፉ የዝናብ ስርጭት እንደሚሆን ይጠበቃል። በክልሉ የሚኖረው የዝናብ ስርጭት በአብዛኛው መደበኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለመኸር እርሻው መሳለጥ ዓይነተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በተለይም አርሶና ከፊል አርብቶ አደሩ የግብርና ልማቱን ለማከወንና ለመከታተል ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር መሪ ስራ አስፈፃሚው ገልጸዋል። በአንፃሩ የዝናቡ ዝርጭት በአብዛኛው መደበኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለወባ ትንኝ መራባት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ የወባ በሽታ ሊጨምር ስለሚችል አስፈላጊው ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል ብለዋል። እንዲሁም አልፎ-አልፎ በሚኖረው ከመደበኛ ያለፈ የዝናብ ስርጭት ቅጽበታዊ ጉርፍ ሊከሰት ስለሚችልም ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አቶ ተስፋሁን አስገንዝበዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 6200
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 5719
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 4550
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 4455
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 5597
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 24, 2026 5177
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የመደመር ማሳያ ከሳምንቱ አበይት ክስተቶች መካከል የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች በአሶሳ ከተማ ያስገነቡት የጋራ ሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህንፃ ምረቃ ይጠቀሳል። በክልሎቹ ትብብር የተከናወነው የህንፃ ግንባታ በመደመር እሳቤ የዜጎችን የጋራ ሰላም ለማስጠበቅና የልማት ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ ጥረት ማሳያ ነው።   መርሃ ግብሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) የተገኙበት ነበር። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም ላይ ያተኮረው መድረክ በሶማሌ ክልል ጂግጂጋ ከተማ የተካሄደውና በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ ያተኮረው ፎረምም በእዚህ ሳምንት ዐበይት ጉዳይ ነበር። ፎረሙ የተካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን የተዘጋጀውም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት ነው።   በፎረሙ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ጠቅሰዋል። እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልጽነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑም በቀጣናው ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ ነው ያነሱት። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ምሁራን ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ እንዲያስቀምጡም ያግዛል ብለዋል። የጉባ ላይ ብስራቶች ተግባራዊ ልማት የሳምንቱ የበረራ ቅኝታችን የሚጀምረው ወደ ሶማሌ ክልል ጎዴ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በስፍራው እየተገነባ ያለውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል።   ከጉብኝታቸው በኋላም በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት የመሬት፣ ውሃ እና የሚያለማ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በቂ ሃብት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህን ካሟላን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ማድረግ ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የኒውክለር ሃይል ማመንጫ፣ የቢሾፍቱ አየር መንገድ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የቤቶች ልማት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጓቸው የጉባ ብስራቶች መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀው ስራ ያስጀምሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር።‎ ‎በግራንዴር ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተገነባው ፋብሪካ፣ መሰረት ልማቱ በ300 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ፣ የዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የሴራሚክና የፎርሲሌን ንጣፎች ማምረቻ ፋብሪካ ነው። የፋብሪካው መገንባት የውጭ ምርት ጥገኝነት ከመቀነስ ባለፈ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑ ታውቋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ ጉብኝት በዚሁ ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ወደ ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጓዝ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በድሬዳዋ ቆይታቸው ብርቱካንና ሌሎች የፍራፍሬ ልማት ሥራዎች እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ልማት ስራን ተመልክተዋል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የግብርና ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባስተላለፉት መልእክትም የጋራ ሙለታ ተፈጥሯዊ የልማት ፀጋና ከፍታም ታሪክን፣ ውብ መልክዓ ተፈጥሮን የታደለ፣ የኢትዮጵያን ሜዳና ተራሮች ምርት የሚታፈስባቸው የማድረግ ሀገራዊ ጉዞ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።   የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ማሳያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ ተገኝተው 142 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ ያስጀመሩትም በዚህ ሳምንት ነበር። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በለውጡ ዓመታት ከልማት የራቁ አካባቢዎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ መሰራቱን አንስተዋል። የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የንጽህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶች ለዚሁ ማሳያ ናቸው ብለዋል።   በተመሳሳይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ እና የመስኖ ፕሮጀክቶች መርቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል።   የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በተለይ አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልት የሚያስቀር ነው። የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።   በሲዳማ ክልልም በፌደራል መንግስት ድጋፍ በ460 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታም ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 75 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ነው።   በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከ543 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 52 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መመረቃቸው ሌላው የሳምንቱ ክስተት ነበር። በዞኑ ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትንም መርቀዋል።   ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግበት የሃዋሳ ከተማ ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም በዚህ ሳምንት ተካሂዳል። ለፕሮጀክቱ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ናቸው፡፡   የፕሮጀክቱ ግንበታ ሲጠናቀቀ ሀዋሳ ከተማዋን ጽዱ በማድረግ የቱሪዝምና የኢንቨስመንት ማዕከልነቷን ያሳድገዋል ተብሏል። አቶ ደስታ የፕሮጀክቱ ግንባታ መንግስት ለከተሞች እድገት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉም ነው የጠቀሱት። የከሰም መስኖ ግድብ የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክትም በዚሁ ሳምንት ተመርቆ ሥራ ጀመሯል። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ነው። የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ያስቀራል ተብሏል።   በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብርሃም (ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር። የጥገና ማሻሻያው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን ይህን የአደጋ ስጋት በማስቀረት ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል የሚያስችል ነው። ለፕሮጀክቱም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ሚኒስትሩ አንስተዋል።   የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል። የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የሀዝቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም አንስተዋል። የግንቦት - ታላቁ ሁነት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ሂደቱን ስኬታማ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አጠቃላይ ዜጎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ።   በዚሁ ሳምንት "ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የመገናኛ ብዙሃን ሚ ና" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአዳማ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎና የዳበረ የዴሞክራሲ ልምምድ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅም መገናኛ ብዙሃን የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ከተረጅነት የመውጣት ሀገራዊ ጥረት በድሬዳዋ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረክም ሌላው የእዚህ ሳምንት ዓቢይ ጉዳይ ነው። መድረኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የግብርና ሚኒስቴር በመተባበር ያዘጋጁት ነው። በመድረኩም በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተነስቷል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቂና የተሟላ የውሃ ሀብት፣ የተማረና አምራች የሆነ ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም ለም የመሬት ፀጋዎች ያሉባት ሀገር በመሆኗ በማልማት እድገትና ማንሳራራትን ማስቀጠል ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል።   ለእዚህም ዋናው መሠረታዊ ጉዳይም ያሉ አቅሞችን በመለየትና ህዝብን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ በማሸጋገር በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጡን ሥራ በላቀ ደረጃ ማስቀጠል መቻል መሆኑን አንስተዋል። ለሰላም ጥሪ የተሰጠ ምላሽ የሠላም ጥሪን የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም (ዲዲአር) መርሀግብርም በዚህ ሳምንት ተከናውኗል። በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል ጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ ሆነው የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።   ታጣቂዎቹ ሠላምን አማራጭ በማድረግና የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፣ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል።   በተመሳሳይ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የክልሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮምቦልቻ የስልጠና ማዕከል ስልጠና የጀመሩ መሆኑ ይታወቃል። ሐረር- ፕሮጀክቶች ምረቃ የሐረሪ ክለል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙትን የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝትም ሌላው የእዚህ ሳምንት ኩነት ነበር። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተሻለ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ።   በተለይም የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መገንባት የክልሉን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የበለጠ በማሳደግ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት። በዘመናዊ ትምህርት የታነፀና በእውቀት የበለፀገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማፍራት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቶቹ በፍጥነትና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ለማስቻል በአስተዳደሩ በኩል ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት 672 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በይፋ የተመረቀውም በዚህ ሳምንት ነው። በምረቃው ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን፣ የክልሉ የመንገዶች ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢድሪስ ሙሴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል።   የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እንደገለጹት ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የከተማውን የንግድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያስችል ነው። የከተማውን ገፅታ በመለወጥ ረገድም የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ነው ያነሱት። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገድ ፕሮጀክቱ የጂግጂጋ ከተማን ልማትና ዕድገት በማፋጠን በኩል ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን አስተዳደሩ ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ዕቅድን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል።   የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 30 ሜትር ስፋት እንዳለውም ታውቋል።  
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 4766
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 4994
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል።   በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል።   በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል።   የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።      
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Jun 7, 2026 1868
ባሳለፍነው ሳምንት … ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባሳለፍነው ሳምንት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተካሂዷል። ድምፅ ለመስጠት 54 ሚሊየን 57 ሺህ 861 መራጮች መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማሳወቁ ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለመራጮች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምርጫው ወቅት ድምጽ ስለሰጡ መራጮች ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ መሆኑን ገልጸዋል። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ማገልገል መታደል መሆኑን ገልጸው፤ ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይህንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ ሲሉም አስገንዝበዋል። ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ሥራ አስጀምረዋል። ‎ ‎በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፕሮጀክቱ ‎በአጠቃላይ 22 ነጥብ 25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን ይሸፍናል። ይህ ፕሮጀክት የማይቆራረጥ የልማት ሥራችን ኅያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሀገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና 73 አባላት ከያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ለዲሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎትና አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን ብለዋል። ‎ ዲሞክራሲያዊ ሂደቶች ከአኅጉራችን ነባራዊ ሁኔታና ተሞክሮ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ አፍሪካዊ ተቋማት ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የምርጫ ሂደታችንን ለመደገፍ በመላው ሀገሪቱ ታዛቢዎችን በማሰማራት የምርጫ ታዛቢ ልዑኩ ላደረገው ያልተቆጠበ ጥረት እውቅና እና አድናቆት እየሰጠን፤ የምልከታውን የተሟላ ውጤት እንጠብቃለን ሲሉም አመላክተዋል። የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻ ልማት፤ የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳን የያዘ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ‎ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ባለው መስመር የሚከናወነው መጠነ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽንም፤ ከወንዞቹ ባሻገር እስከ 50 ሜትር የሚዘልቅ መሆኑን አስረድተዋል። የአረንጓዴ ኮሪደሮችን፣ የሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን እና የንግድ ቦታዎችን ልማት ማካተቱን ጠቅሰው፤ ከተማዋን በእጅጉ የቀየረ ነው ብለዋል። ‎ የወንዝ ዳርቻዎችን ገጽታ እና አገልግሎት ከማሻሻል ባለፈ በኮንስትራክሽን፣ በኢንጂነሪንግ፣ በመልክዓ-ምድር ውበት ግንባታ፣ በሎጂስቲክስ እና በተያያዙ ዘርፎች ለብዙ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም አብራርተዋል። አብዛኛው ሥራ በሀገር ውስጥ መሐንዲሶች መቀረጹና መተግበሩ፤ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በከተማ ልማት እና በመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸው ዐቅም እያደገ መምጣቱን ያሳያል ነው ያሉት። ‎ ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎች እና ቆሻሻዎች የሚጣሉባቸው፣ በወንዝ ዳርቻዎች በሚኖሩ ማኅበረሰቦች ላይ የጎርፍ አደጋ ይጋርጡ የነበሩት እነዚህ አካባቢዎች፤ አሁን ላይ ወደ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ለሕይወት ምቹ ወደሆነ የከተማ ቦታነት እየተቀየሩ መሆኑንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ ሁኔታም፤ የንግድ እና የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ተቀናጅተው መገንባታቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ከዚህ ቀደም ከነበረው ያልተናበበ ሥራ ተላቀው በጥናትና በጋራ ግብ ተባብሮ መሥራት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ስለመሆኑ አመላክተዋል። ‎ይህ ፈጣን የልማት ሥራ አዲስ አበባን አረንጓዴ፣ ይበልጥ የተሳሰረች፣ በኢኮኖሚ ንቁ እና ሰውን ማዕከል ያደረገች ከተማ የማድረግ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ላይ መሰረት የተጣለበት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ
በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ …
Jun 3, 2026 2604
በዮሐንስ ደርበው በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር ሞላወርቅ አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በዓለምም ሆነ በሀገራችን አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው የደም ግፊት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በቆይታቸውም፤ ለደም ግፊት አጋላጭ ስለሆኑ ምክንያቶችና ሊደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄም እንዲሁም ከመድሃኒት አወሳሰድ ጋር በተያያዘ ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን አቅርበዋል። · የደም ግፊት ምንድን ነው? ደም በደም ሥሮቻችን ሲያልፍ፤ የሚለካው መጠን “የደም ግፊት” እንደሚባል ዶክተር ሞላወርቅ ያስረዳሉ። የላይኛው (ሲስቶሊክ ወይም ከፍተኛው) የደም ግፊት መጠን ልብ በምትኮማተርበት ጊዜ ደም ወደ ደም ሥር ሲረጭ የሚለካው መሆኑንም ይገልጻሉ። የታችኛው (ዲያስቶሊክ ወይም ዝቅተኛው) የደም ግፊት መጠን ደግሞ ልብ ደም ለመቀበል ለአፍታ ዕረፍት በምታገኝበት ጊዜ የሚከሰት የግፊት ደረጃ መሆኑንም ይገልጻሉ። · የደም ግፊት ደረጃዎች እና ማስጠንቀቂያቸው ዶክተር ሞላወርቅ እንደሚሉት፤ የጤናማ ሰው የደም የግፊት መጠን 120 በ 80 እና በታች መሆን ይኖርበታል። በሌላ በኩል ግን ይላሉ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 የታችኛው ደግሞ ከ80 በታች ከሆነ “ከፍ ያለ ወይም የጨመረ የደም ግፊት ደረጃ” ይባላል። የላይኛው ከ130 እስከ 139 ወይም የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከሆነ ደግሞ “ደረጃ አንድ የደም ግፊት” እንደሚባል ያስረዳሉ። የላይኛው ከ140 በላይ ሲሆን እና የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ ደግሞ “ደረጃ ሁለት የደም ግፊት” እንደሚባል ነው የሚገልጹት። በሌላ በኩል “የከፋ የደም ግፊት ደረጃ” የሚባል እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም የላይኛው ከ180 በላይ እና የታችኛው ከ120 በላይ ሲሆን ነው በማለት ያብራራሉ። · ለደም ግፊት መጨመር መንስዔዎቹ ምንድን ናቸው? በዋናነት ሁለት ዓይነት የደም ግፊት መኖሩን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ ከፍተኛ የደም ግፊት እና መንስዔው የሚታወቅ የደም ግፊት መሆኑን አስረድተዋል። በዋናነት ወይም በአብዛኛው ከ90 እስከ 95 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ ደም ግፊት የሚባለው መሆኑን ገልጸው፤ በርካታ መንስዔዎች ሊኖሩት እንደሚችሉ ቢገመትም ሁሉም በውል እንደማይታወቁ ያነሳሉ። ከበርካታ መንስዔዎቹ መካከልም፤ በቤተሰብ የሚወረስ (ተላላፊ)፣ አካባቢያዊ ምክንያቶች እንዲሁም የአኗኗር ዘይቤ የሚሉት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። የአኗኗር ዘይቤ ሲባልም፤ የአመጋገብ ሥርዓት በተለይም ጨው የበዛበት ምግብ፣ ክብደት መጨመር፣ አካባቢያዊ ሁኔታዎች (አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ)፣ የስኳር ታማሚ መሆን የሚሉት ይጠቀሳሉ ይላሉ። · ለደም ግፊት በተለይም እነማን ተጋላጭ ናቸው? ዕድሜ በጨመረ ቁጥር የደም ግፊት የመከሰት ዕድሉም እንደሚጨምር ጠቅሰው፤ በዚህም መሠረት ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ተጋላጭ መሆናቸውን ይናገራሉ። እንዲም በቤተሰብ የደም ግፊት ኬዝ ያለባቸው ሰዎች፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒክ ግሩፕ) ለምሳሌ፡- በጥቁሮች (አፍሪካውያን)፣ በኤስያውያን፣ በደቡብ ኤስያውያን ላይ ከፍተኛ የደም ግፊት ሊከሰት እንደሚችል ይገልጻሉ። እንደ ዶክተር ሞላወርቅ ማብራሪያ፤ በአጠቃላይ አጋላጭ ምክንያቶች በሁለት ተከፍለው ሊታዩ ይችላሉ። አንደኛው፡- ልንከላከላቸው (ልንቀንሳቸው) የምንችላቸው መሆናቸውን በመግለጽ ይህም የአመጋገብ ሥርዓትን ማስተካከል፣ ክብደት መቀነስ፣ አልኮልና ሲጋራ ማቆም እና መሰል መሆናቸውን አብራርተዋል። ሁለተኛው፡- ልንከላከላቸው የማንችላቸው መሆናቸውን ገልጸው ይህም፤ የዕድሜ መጨመር፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒሲቲ) እና በቤተሰብ የሚተላለፍ የሚሉትን ጠቅሰዋል። · የደም ግፊትን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? የደም ግፊ ከተከሰተ መቆጣጠር እንጅ ማዳን እንደማይቻል ገልጸው፤ ከላይ እንደተጠቀሰው አስቀድሞ መከላከል ወይም ማዘግየት የሚቻል እና መከላከል የማይቻል የደም ግፊት ደረጃ መኖሩን አስረድተዋል። · የደም ግፊት በውል የሚታወቅ ምልክት አለው? የደም ግፊት ሲከሰት ምልክት እንደሌለው በማንሳት፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ “ዝምተኛው ገዳይ” እስከመባል መድረሱን ዶክተር ሞላወርቅ ያነሳሉ። ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ግን፤ በአንድ ወይም በሁለት የሰውነት አካል ላይ ችግር ሊደርስ እንደሚችል ከዚህም ሲያልፍ እስከ ሞት እንደሚያደርስ ይጠቅሳሉ። በተያያዘም፤ የራስ ምታት፣ የዐይን ብዥ ብዥ ማለት፣ ትንፋሽ ማጠር፣ የድካም ስሜት፣ አንገት የመያዝ ዓይነት ስሜቶች የደም ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ሊስተዋሉ የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል። አክለውም፤ በአብዛኛው በሕብረተሰቡ ላይ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከፍተኛ ደረጃ ይደርስና ድንገት በጨመረ ጊዜ፤ ለሞት፣ ለአደጋ፣ ለልብ ድካም፣ አጣዳፊ ለሆነ የልብ ህመም፣ በጭንቅላት ላይ የደም መፍሰስ፣ የኩላሊት ድክመት፣ በደም ሥሮች በአግባቡ ደም እንዳይተላለፍ ማድረግ፣ ለዐይነ ስውርነት መዳረግን ጨምሮ መሰል ጉዳቶችን ሊያስከትል እንደሚችል አስገንዝበዋል። · መድኃኒት አወሳሰድ ላይ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ ዶክተር ሞላወርቅ እንደገለጹት፤ አንድ ሰው ደም ግፊት እንዳለበት ከተነገረው በኋላ ሕክምናውም እንደ ደም ግፊቱ ደረጃ ይለያያል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 ከሆነ “የጨመረ ግፊት” ይባላል፤ እዚህ ላይ ሰውየው ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ አመጋገቡን እንዲያስተካክል፣ ስፖርት እንዲሠራ፣ ክብደት እንዲቀንስ፣ ሱስ (ሲጋራ፣ አልኮል) እንዲቀንስ ክትትል ይደረጋል ብለዋል። ስለዚህ መድኃኒት ሳይጀምር የአኗኗር ዘይቤን በማስተካከል የደም ግፊቱን ሊቀንሰው (ሊቆጣጠረው) ይችላል ማለት ነው ሲሉም ይገልጻሉ። “ደረጃ አንድ ግፊት” የሚለው ላይ ከደረሱ ግን ሕክምና የሚጀምሩም የማይጀምሩም እንዳሉ ተናግረዋል። ይህም ማለት የላይኛው ከ130 እስከ 139 የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከደረሰ ሕክምና የሚጀምሩት የስኳር ህመም ያለባቸው፣ የስትሮክ ህመም ያለባቸው፣ ከልብና ደም ሥር የተገናኙ ህመሞች ያሉባቸው ከሆኑ ቢያንስ አንድ የግፊት መድኃኒት መጀመርና ክትትል ማድረግ አለባቸው ይላሉ። በሌላ በኩል ግን ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ ሰዎች “ደረጃ ሁለት ግፊት” ላይ ከደረሱ (የላይኛው ከ140 የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ) ሁሉም መድኃኒት መጀመር እንዳለባቸው በአጽንዖት ገልጸዋል። የሚጀምሩት መድኃኒትም አሁን ባለው በተሻሻለው የሕክምና ዘይቤ ሁለት መድኃኒቶች የሚጀምሩበት ሁኔታ እንዳለ ነው የሚያስረዱት። የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል ግን ለሁሉም የግፊት ዓይነቶች መሠረት (የሚመከር) መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ መድኃኒት ጀምሬያለሁ ብሎ የአኗኗር ዘይቤው ላይ ቸልተኝነት ሊኖር እንደማይገባም ነው የሚመከሩት። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከግፊት ጋር በተያያዘ ወደ ሆስፒታል መጥተው የሚታከሙ ታካሚዎች አብዛኞቹ፤ ጀምረው ያቋረጡ፣ ለመጀመር ፍላጎት የሌላቸው፣ ቅድመ ምርመራ ባለማድረግ ምክንያት ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ የተጎዱ ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። ስለዚህ የግፊት መድኃኒት ከተጀመረ ሊቋረጥ እንደማይችል አስጠንቅቀዋል። በየጊዜው ክትትል ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በሂደት እንደ ግፊቱ ሁኔታ መድኃኒቶች ሊቀነሱም ሊጨመሩም እንደሚችሉ አመላክተዋል። · የመስፋፋት ደረጃ የዓለም ጤና ድርጅት በ2024 ያወጣውን መረጃ ዋቢ አድርገው፤ 1/3ኛው የዓለም ሕዝቦች በደም ግፊት እንደሚጠቁ ዶክተር ሞላወርቅ አንስተዋል። ከእነዚህ መካከልም፤ 7 ነጥብ 6 ሚሊየን ገደማው በአንድም በሌላም ምክንያት ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ጠቁመዋል። አብዛኞቹ የደም ግፊት ታማሚዎች ቁጥር የሚመዘገበው ደግሞ በመካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ሀገራችንን ያካትታል ሲሉ ገልጸዋል። በሀገራችን ደረጃም ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ባይኖሩም ከግፊት ጋር በተያያዘ በ2001 ላይ በ35 ሳይቶች የተጠኑ ጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከ21 እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ በደም ግፊት የሚጠቃ ነው ይላሉ። በአብዛኛው ደግሞ ከተማ ላይ እንደሚበዛ ጠቁመው፤ በተለይም አዲስ አበባ ላይ እስከ 30 በመቶ እንደሚደርስ የጥናቶቹ ውጤቶች ማመላከታቸውን ተናግረዋል። አብዛኞቹ ኬዞች ደግሞ ዕድሜያቸው ከፍ ያለ፣ ክብደታቸው የጨመረ፣ አልኮል እና ሲጋራ የሚጠቀሙ እና የስኳር ህመም ያለባቸው ሰዎች ጋር የሚገናኙ መሆናቸውን አስረድተዋል። እንደ ዓለም አቀፍ ደረጃም ኬዙ ካለባቸው መካከል ግማሽ ያህሉ ግፊት እንዳለባቸው እንኳን እንደማያውቁ ነው የሚገልጹት። ለግፊት ሕክምና ትክክለኛ ክትትል አድርገው ግፊታቸውን በአግባቡ የሚቆጣጠሩት ከ 5 ሰዎች 1 መሆኑንም ጥናቶች ያሳያሉ ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ በሀገራችን በሕብረተሰቡ ዘንድ ለደም ግፊት መለካት ኬዙ ከተገኘም የሕክምና ክትትል የማድረግ ሁኔታዎች ዝቅተኛ መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ሕብረተሰቡ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከአካል ጉዳት እስከ ሞት ሊያደርስ እንደሚችል ተገንዝቦ፤ የደም ግፊቱን የመለካት ልምምዱን ሊያዳብር እንደሚገባ ዶክተር ሞላወርቅ መክረዋል። በሌላ በኩል እንደ ሀገራችን ባሉ ሆስፒታሎች በጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ ወይም መቋረጥ (ስትሮክ) ካለባቸው ሰዎች ከ70 እስከ 85 በመቶው ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ የሚከሰት መሆኑን ገልጸው፤ ድንገተኛ ግፊት መጨመር ከልብ እና ከደም ሥሮች ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዓለምም ሆነ እንደ ሀገር አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንደኛው ግፊት መሆኑንም አረጋግጠዋል። ስለዚህ የደም ግፊትን መለካት፣ የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል፣ ከሱስ መራቅ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር ለጤናማ ሕይወት ከፍተኛ ሚና እንዳለው መክረዋል።  
 ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት
May 24, 2026 5738
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኝ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአንጀት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች በውል ይታወቃሉ? ቀድሞስ መከላከል ይቻላል? የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። ለምን ቢሉ? ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ስላለው ይሆናል መልሱ። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫዎት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁንእንጅ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል።ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚህ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዐለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዐለም ዐቀፍ፣ አኅጉር ዐቀፍ እና ሀገር ዐቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ይህም ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫዎታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል። #የኮሪደር_ልማት #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 3465
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ‎ ‎​ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። ‎ ‎መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ‎ ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 12972
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 7241
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 13017
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 11483
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 78123
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 63726
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 44097
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 41671
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 32395
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 31840
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 31318
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 30616
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 78123
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 63726
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 44097
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 41671
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 5597
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 6225
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም