ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በአፋር ክልል የጠቅላይ ፍርድ ቤት አሰራሮችን በማቀላጠፍ የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ ተችሏል
Aug 9, 2026 32
ሰመራ፣ ነሀሴ 3/2018 (ኢዜአ)፡-በአፋር ክልል የጠቅላይ ፍርድ ቤት አሰራሮችን በማቀላጠፍ የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሙሳ አብዶ ገለጹ። የአፋር ክልል ምክር ቤት 6ኛ የምርጫ ዘመን፣ 5ኛ የሥራ ዘመን፣ 10ኛ መደበኛ ጉባዔውን በማካሄድ ላይ ነው። በዛሬ ሁለተኛ ቀን ውሎው የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሪፖርት ፕሬዚዳንቱ ሙሳ አብዶ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ዲጂታላይዜሽን አሰራርን በመተግበር የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ ተችሏል። ይህም በፍርድ ቤቶች የነበረውን የሥራ ጫና ማስቀረቱን ተናግረው፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለአቤቱታ ከቀረቡ 14 ሺህ 309 መዝገቦች ውስጥ ከ13 ሺህ በላይ መዝገቦች ውሳኔ አግኝተዋል ብለዋል። በእዚህም አፈጻጸሙ 97 ከመቶ መሆኑን የገለፁት አቶ ሙሳ፣ ካለፈው ዓመት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የሦስት ከመቶ ብልጫ አለው ብለዋል። ለውጤታማነቱም ተከታታይነት ያላቸው የክትትልና የድጋፍ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። በፍርድ ቤቶች የሚሰጡ አገልግሎቶች ጥራትና ፍጥነት እንዲኖራቸው አሰራርን ከማዘመን ባለፈ የሰው ሀይሉን ለማብቃት መሰራቱንም ፕሬዚዳንቱ አመልክተዋል።
የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች የወጣቶችን ስብእና የመገንባት ሚና አላቸው
Aug 9, 2026 49
ደብረ ብርሃን፤ ነሐሴ 3/2018(ኢዜአ)፡-የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች የወጣቶችን ስብእና ለመገንባት ሚና እንዳላቸው የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ውድድርን ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ አስጀምሯል። የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ በዚህ ወቅት እንደገለጹት ከተማዋን የቱሪዝም፣ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማእከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። በተለይም የስፖርት ዘርፉን በማሳደግ ጤናማና አምራች ዜጋ ለማፍራትና በሀገር እና ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ወጣቶችን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማ አስተዳደሩም ባለሀብቱንና ማህበረሰቡን በማስተባበር በየጊዜው የሚካሄዱ የታዳጊዎች ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድርን በልዩ ትኩረት እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል። በክረምት ወቅት ወጣቶች ገዜያቸውን የሚያሳልፉበትን ስፖርታዊ ውድድር ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ የተጀመረው ውድድርም የዚህ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ተክለዮሐንስ ኃይለጊዮርጊስ በበኩላቸው የክረምት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች ታዳጊዎች የእረፍት ጊዜያቸውን በአልባሌ ስፍራ እንዳያሳልፉ ለማድረግ ታስቦ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። ዛሬ በተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች እግር ኳስ ውድድር በ60 ቡድኖች የታቀፉ 1ሺህ 500 ስፖርተኞችን በማሳተፍ የሚካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። የውድድሩ ዓላማ ወጣቶች በስፖርታዊ ስነ ምግባር ከመታነጽ ባለፈ ተሰጧቸውን አውጥተው በማሳየት በቀጣይ ለትልልቅ ክለቦች የሚመረጡበትን እድል የሚከፍት ነው ብለዋል። በተለይም ስፖርት ለሰላምና ለአንድነት ያለውን አበርክቶ በመጠቀም ወጣቶች አንድነታቸውን በማጠናከር ለአካባቢያቸው ሰላምና ልማት በጋራ እንዲሰለፉ ለማድረግ እንደሚካሄድ አስረድተዋል። "የኮኮብ እግር ኳስ ቡድን" አሰልጣኝ ሐብታሙ መለሰ፣ የክረምት ውድድር መዘጋጀቱ ታዳጊዎች በስልጠና ያገኙትን የቴክኒክ እውቀት በተግባር የሚያሳዩበት ዕድል ይፈጥርላቸዋል ብለዋል። "የአንድነት እግር ኳስ ቡድን" አሰልጣኝ ታምራት ደስታ በበኩላቸው ውድድሩ የባህል ልውውጥ በማድረግ አንድነትንና መተሳሰብን ለማጎልበት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል በደብረ ብርሃን ከተማ ዛሬ የተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ውድድር ለአንድ ወር የሚካሄድ መሆኑ ተመላክቷል።
ቀልጣፋ የአሰራር ስርዓት በመተግበር አልሚዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለመሳብ ተችሏል
Aug 9, 2026 98
ጋምቤላ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦ሀገሪቱ ያሏትን የኢንቨስትመንት እድሎች ለባለሀብቶች የማስተዋወቅ እና አገልግሎቶችን ቀልጣፋ የሚያደርጉ አሰራሮችን በመተግበር በርካታ አልሚዎችን ወደ ሀገር ውስጥ መሳብ መቻሉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለጸ። የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈፃሚ አካላት በጋምቤላ ከተማ እያካሄዱት ባለው የጋራ ምክክር በ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምና በአዲሱ በጀት ዓመት እቅድ በመምከር የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዳጋቶ ኩምቤ በመድረኩ ላይ እንዳሉት የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ አልሚዎችን ለመሳብ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስገኙ ነው። በዚህም በበጀት ዓመቱ ብቻ 528 የውጪ ሀገር ባለሃብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ''ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ 2026 ፎረም’’ የኢንቨስትመንት ስምምነትንም የፈረሙ ሰባት ተቋማት 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ካፒታል ፈሰስ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣይም የዲጂታል አገልግሎቱን በማስፋትና ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጠናከርና የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ተመራጭነት ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የኮሚሽኑ የስፔሻል ኢኮኖሚ ዞን ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ዝናቡ ይርጋ በበኩላቸው፥ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ወደ ውጤት በመቀየር የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራሩ ይጠናከራል ብለዋል። ለዚህም የመሰረተ ልማት አውታሮችን ተደራሽነት የማስፋትና የአሰራር ማእቀፎችን ማስፋት ላይ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የሚተገበር መሆኑን ተናግረዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፥ ባለሃብቶች ለሚያጋጥማቸው ተግዳሮቶች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ቅንጅታዊ አሰራሮችን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። የምክክር መድረኩ በ2018 እቅድ አፈፃፀምና በአዲሱ በጀት ዓመት ውይይት በማድረግ የትኩረት አቅጣጫ ያስቀመጠ ሲሆን ተሳፊዎች በዛሬው ዕለት ከጋምቤላ ክልል ርዕሰ መሰተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ጋር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። በቀጣይም የልማት ምልከታ የመስክ ጉብኝት በማካሄድ መርሃ ግብራቸውን እንደሚያጠናቅቁ ይጠበቃል።
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር!
Aug 9, 2026 151
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር! በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን ) የገጠሩ ማህበረሰብ የጨለማ ኑሮ የተፈረደበት ይመስል ኑሮውን ማሻሻል ሳይችል እልፍ ዓመታት ተቆጥረዋል፤ ለዘመናት መብራትና ውኃ ለማግኘትና ከቴክኖሎጂ ጋር ተቀራርቦ ለመኖር ወደ ከተማ መሰደድ ብቸኛው አማራጭም ነበር። የከተሜው ዋልታ የሀገር ኢኮኖሚ መሠረት የሚወሰንበት የአራሹ ገበሬ የኑሮ ደረጃ ባህላዊውን የአኗኗር ዘዬ ባለመልቀቁ ደስተኛ ጊዜ የሚያሳልፍበት ሂደት አድካሚ እንደሚሆን ግልጽ ነው። የገጠሬው የተበታተነ የአኗኗር ሥርዓትም ለገጠሬው አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፤ የእዚህን የህብረተሰብ ክፍል ምርቱን እንጂ ኑሮውን የጠየቀ አልነበረም ቢባል ግነት አይሆንም። ቀደም ሲል በነበሩ መንግስታት ከተማን እንጂ ገጠርን ማዘመን የሚያስብ ስለመኖሩ ያጠራጥራል፤ ይህም በሀገሪቱ ለኢፍትሐዊ ዕድገት የራሱን ተጽዕኖ ሲያሳደር ቆይቷል። የመደመር መንግሥት ግን ይህን ቀይሮታል። ሀገር የመምራት ኃላፊነት ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ በከተማና በገጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ በዜጎች የኑሮ ሥርዓት ላይ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርጎ እየሰራ ነው ከተሜነት ብቻውን አድጎ የገጠሩ ማኅበረሰብ በቀድሞ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሆነ የተሟላ ዕድገት ማምጣት አይቻልም የሚል ጽኑ እምነት አለው። በእዚህም ከተማና ገጠርን ለማቀራረብ በገጠር ትራንስፎርሜሽንን የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ቀርጾ መተግበር ከጀመረ ከራርሟል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን አንዱ አካል የሆነው የገጠር ሞዴል መንደር በአርሶ አደሮች ዘንድ የሚጨበጥ ተስፋን ይዘው ከመጡ ኢኒሼቲቮች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው። ከተስፋ ተሻግረው በዚህ ሞዴል መንደር የነዋሪነት ዕድልን ያገኙት ደግሞ ብርሃን አይተዋል፤ የትናት አኗኗራቸውን የቀየረ አዲስ ዛሬን በእጃቸው አድርገዋል፤ ነገን አልቀው መመልከት የግብርና ተግባራቸው አንዱ አካል ሆኗል። በአዲሱ መንደራቸው ዛሬ የሚያፈስ ቤት የለም፣ የእንስሳት ቆሻሻ ሽታ በአፍንጫቸው አይገባም፣ በሚቆረቁር እንጨት ወይም መደብ ላይ አይቀመጡም፤ የከተሜው መዘነጫ ሶፋ በሳሎናቸው ተከስቷል። ጓሮዎቻቸው ሁሉ ሙሉ እንደሆኑ አፍ አውጥተው የሚያወሩ ናቸው። በዚህ ቆስጣ፤ በዛ በኩል ጎመንና ቀይስር፤ ዘውር ሲሉ ደግሞ ከአስር የሚልቁ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፤ በአንድ ክፍል ደግሞ እናት ላም ከጥጃዋ ጋራ፣ የእንቁላል ዶሮ ከሥጋ ዶሮ ጋር ሁሉንም በአንድ ጊቢ ውስጥ ያገኛሉ። ምን ይሄ ብቻ አቮካዶ እና ፓፓያ፣ ሙዝና እንሰት፣ በርበሬና ሽንኩርት ሳይቀር ለተትረፈረፈ የአርሶ አደር ማዕድና ገበያ ራሳቸውን አዘጋጅተዋል። አርሶ አደር ኃይሉ ሞትንሞስ በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የጌሊት ሞዴል መንደር ነዋሪ ናቸው። እርሳቸው "መንግስት ጨለማችንን ገፎ ብርሃን አሳየን" ሲሉ በጠንካራ ቃላት የገጠር ሞዴል መንደር ፕሮጀክት ያመጣላቸውን በጎ ነገር ይገልጻሉ። እውነት ነው ያላዩትን ብዙ ነገር አሳይቷቸዋል። ያም ብርሃን ቤት ውስጥ የሚበራ ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው፣ በነገ ተስፋቸውና በኢኮኖሚያቸው ላይ የፈነጠቀ ብርሃን ነው። ዛሬ ያሉበትን ህይወትም "ለእኔ አዲስ ነገር ነው። አይቼው አላውቅም፤ መቼም በራሴ ሀሳብ አላደርገውም ነበር።" ሲሉ ይገልጻሉ። መንግስት አበራልኝ ያልኩት በእጄ ያለኝን ያላየሁትን ዕድል ስላሳየኝ ነው በማለትም ሀሳባቸውን ይቀጥላሉ። እኛ ሀብት አለን፤ ሀብታችንን የምንጠቀምበት መንገድ ግን ትክክል አይደለም። ይልቁንም የምናባክነው ይበዛል በማለትም የቀደመ ሕይወታቸውን እያሰቡ ይቆጫሉ። አሁን ግን ብዙ ተገነዘብኩ የሚያስብል የመደመር መንግስት በመኖሩ አዲስ ሕይወት በአዲስ ተስፋ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። እርግጥ ነው የገጠር ሞዴል መንደር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ነው። ለአብነትም የማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ መሠረተ ልማት ዝርጋታን ማንሳት ይቻላል። የተሠሩ ሞዴል መንደሮች በመጀመሪያ የመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ የመሆን ዕድል ገጥሟቸዋል። በመቀጠል ንጽሕናው ያልተረጋገጠ የመጠጥ ውኃ ወንዝ ወርዶ ከመቅዳት ተቆጥበው በመንደራቸው የተገነባውን የከረሰ ምንድር ውሃ ከቧንቧ ቀድተው መጠጣት አስችሏቸዋል። በእሳት እና ኩራዝ ጭስ ሲሰቃዩ የነበሩ ዓይኖቻቸው ዛሬ ከሶላር ቴክኖሎጂ የመነጨ ብርሃን ማየት ጀምረዋል። ብርሃን ብቻ አይደለም ለወትሮ ለገበያ ወደ ከተማ ብቻ ሲወጡ ይመለከቱ የነበረውን ቴሌቪዥን ዛሬ በቤታቸው አስገብተው የመረጃና የመዝናኛ ዓለምን ተቀላቅለዋል። አርሶ አደሮቹ ቴሌቭዥንን ከመዝናኛነት ይበልጥ ለመረጃ እንደሚጠቀሙት ያነሳሉ። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በዜና ተከታትሎ መረዳት፣ የገበያ ሁኔታን ማወቅ፣ የግብርና ሥራ ተሞክሮን መቅሰምና የአየር ንብረት ሁኔታን ጨምሮ ለሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙት ከቴሎቪዥን መስኮት እንደሆነ ይናገራሉ። በጓሯቸው የተትረፈረፈ የሌማት ትሩፋት ምርት መሰብሰብ የሚያስችላቸው ምቹ ሁኔታ ደግሞ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው። በተለይ መንግስት በጓሯቸው ጥምር እርሻ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ የነገ ኢኮኖሚያቸውን በአስተማማኝ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ ነው። ከተማን መናፈቅን ያስቀረው የገጠር ሞዴል መንደር ያኔ ከጅምሩ አመኔታን አላገኘም። የቦታና የአካባቢ ቁሳቁስ ለማቅረብ ዝግጁ እስካለመሆን የደረሱ አርሶ አደሮችም ነበሩ። በወቅቱ ጉዳዩን እንደፌዝ አዩት። ዛሬ ግን ውጤቱን በአግራሞት በዐይናቸው ተመለከቱ። የተናገረውን የሚከውን፤ የጀመረውን የሚጨርስ የመደመር መንግሥትን ተጨባጭ ስራዎች በማረጋገጥ እንደ ትንግርት ቆጠሩ። ዛሬ በየአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች በቁጭት ተሞልተው መንደራቸውን ወደዚህ የሞዴል መንደር እሳቤ ለመቀየር ተነሳስተዋል። የጌሊት ቀበሌ አርሶ አደሮቹ መኮንን አርዶ እና ነጻነት ተስፋሁን ለዚህ ተጠቃሾች ናቸው። ያዩትን ተሞክሮ በራስ አቅም በመንደራቸው ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ከተማ ሄደን የምናወጣውን ወጪና የምናባክነውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት እዚሁ መዝናናት የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ብለዋል። "ይህ ዕድል ለእኛ ለአርሶ አደሮች በታሪክ የሚነገር ትልቅ አጋጣሚ ነውም" ይላሉ። በጤዛ እየራስን እንጓዝበት የነበረው መንገዳችን ዛሬ ሰፍቷል። ተሽከርካሪ በደጃችን ስለሚያልፍም ምቹ ዕድልን ይዞልን መጥቷል። ይህን ጅምር ተግባር ወደ ላቀ ውጤት ማሸጋገር የእኛ ድርሻ ነውና ጠንክረን እንሠራለንም ብለዋል። ይህን ዕድል ወደ ትልቅ አቅም ለመቀየር መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳ የሸሸቃ ሞዴል መንደር ተጠቃሚ አርሶ አደር አልዓዛር ዘርክናንስ ናቸው። የዶሮና የከበት እርባታን እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ማነብ ሥራን ከመደበኛው የእርሻ ሥራ ጋር አስተሳስረው በመሥራት ከቤተሰብ ፍጆታ ተርፎ ለገበያ የሚበቃ ምርት ለማምረት እየተዘጋጁ ነው። ይህም የገቢ አቅማቸውን ከማሳደግ ባለፈ ልጆቻቸው ወተትና የወተት ተዋጽኦ በቤታቸው እንዲያገኙ ያደርጋል። ማር፣ እንቁላል እና ሥጋ እንዳያምራቸው የሚያደርግ ትልቅ ኢኒሼቲቭም ነው። አንዱ ቢጎድል በሌላው እየሞሉ የሚኖሩበትን የሥራ መስክ አጠናክረው ለውጤት አብቅተው ለተሻለ ለውጥ እንደሚሠሩ አክለዋል። የአርሶ አደር እናቶች ዘምቢል ይዘው አትክልትና ፍራፍሬ ሸመታ ወደ ገበያ ማቅናት የለባቸውም። ይልቁንም ከጎሮቸው ወደ ገበያ ይዞ መውጣት የኑሮ ዘዬያቸው ወግ ነው። ወይዘሮ መሠረት ማሞ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የበቆ ሞዴል መንደር ነዋሪ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ያልለመዱትን አዲስ ሕይወት ከአዲስ ተስፋ ጋር መጀመራቸውን ከሚናገሩት መካከል ናቸው። ትናንት ኩሽናቸው፣ መኝታቸው እንዲሁም የከብትና የዶሮ ማደሪያ በአንድ ቤት ወስጥ የተወሰነ እንደነበር ያስታውሳሉ። ዛሬ ግን ሽንት ቤትና መታጠቢያ ቤት ሳይቀር ለየብቻ የራሱ የሆነ ቤት ተገንብቶ ጽዳቱ የተጠበቀ ኑሮ መኖር ጀምረዋል። ቤታቸው ሲገቡና ሲወጡ ለዓይን ማራኪ፤ ለመቀመጥ ምቹ፤ ለመተኛትም ንጹህና ወገብ የሚያሳርፍ ሆኖ አግኝተዋል። እናም በዚህ እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ። "መንግስት እንደ አባት ጎዶሏችንን ሞልቷል" ሲሉም ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት ይህ የአርሶ አደሮችን ሕይወት ብሩህ ያደረገው የገጠር ሞዴል መንደር ኢኒሼቲቭ በመላው ሀገሪቱ በመስፋፋት ላይ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 16 ሞዴል መንደሮች በ16 ወረዳዎች ተገንብተዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት ኢኒሺዬቲቩ የአርሶ አደር ኑሮ ዘዬን ከማሻሻል ባለፈ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ ጋር ለማቆራኘት ያስቻለ ነው። የተሻለ መኖሪያ ቤት ኖሮት በጓሮው የሚበላ ነገር ካጣ ሕይወቱ ትርጉም ያለው ለውጥ አያመጣም። ይህም በመሆኑ ቤቶቹን ከእያንዳንዱ የግብርና ልማት ዘርፎች ጋር በማጣመር እንዲገነቡ የተደረገው። ይህም የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል ሀገራዊ ስትራቴጂን የሚያጠናክርና ገበያን የማረጋጋት ዓላማን የያዘ ጭምር ነው። በገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ የተገኘው መልካም ውጤት በቀጣይ በሁሉም ወረዳዎች የሚስፋፋ ሲሆን በዞን እና ወረዳ መዋቅሮች ድጋፍና ክትትል በቀበሌ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አንስተዋል። ይህ ኢኒሼቲቭ የሀገራዊ ብልጽግና ጉዞ አንዱ አቅም ነው። የተደመረ የማኅበረሰብ ብልጽግና ሀገርን ከፍ ያለ የዕድገት ማማ ላይ ያስቀምጣታል። እነሆ የክልሉ አርሶ አደሮች የአካባቢያቸውን ጸጋ ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ የሚቀይሩበት መስክ በሞዴል መንደር ምክንያት እጃቸው ላይ ደርሷል። አርሶ አደሮቹ እንዳሉትም በብዙ መንገድ ጨለማ የከበበው የገጠሩ ማኅበረሰብ ሕይወት ዛሬ ብርሃን ማየት ጀምሯል። ይህ የብርሃን ፋና እየተቀጣጠለ ወደ ብዙኃኑ ሊደርስ የሁሉንም ፍላጎት አነሳስቷል። ሥሩ ከማለት ይልቅ ሠርቶ ማሳየትን የሚያስቀድመው የመደመር መንግስት የፈጠራቸው የገጠር ሞዴል መንደሮች ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን በዘላቂነት የሚያሳምሩ ናቸው። ሰላም እንሰንብት!
የዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ዛሬ ፍጻሜውን ያገኛል
Aug 9, 2026 90
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦ 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጠናቀቃል። ከሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአሜሪካ ኦሬጎን እየተካሄደ ባለው ሻምፒዮና ከ147 ሀገራት የተወጣጡ ከ1800 በላይ አትሌቶች ተሳታፊ ሆነዋል። ኢትዮጵያም በሻምፒዮናው ላይ ተሳትፎ እያደረገች ሲሆን እስከ አሁን ሁለት የወርቅ፣ ሶስት የብር እና አንድ የነሐስ በድምሩ ስድስት ሜዳሊያዎችን በማግኘት ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። አሜሪካ በስምንት ወርቅ፣ ስድስት የብር እና አራት የነሐስ በድምሩ 18 ሜዳሊያዎችን በማግኘት አንደኛ ደረጃን ይዛለች። ጣልያን በሶስት ወርቅ እና ሁለት ነሐስ በድምሩ አምስት ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። እስከ አሁን 35 ሀገራት የሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ ገብተዋል። ሻምፒዮናው ዛሬ ማምሻውን በሄይዋርድ ፊልድ ስታዲየም ይጠናቀቃል።
ፖለቲካ
ብልፅግና ፓርቲ የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ያከናውናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 9, 2026 139
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምፅ ያገኘው ብልፅግና ፓርቲ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እንደሚያከናውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምፅ ያገኘው ብልፅግና ፓርቲ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት በሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ተግባራት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምጽ ያገኘው ብልፅግና ፓርቲ በሚመሰርተው መንግስት በመጪዎቹ አምስት ዓመታት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እንደሚያከናውን ጠቅሰዋል። በሀገር ደረጃ ትልቅ ምክክር እየተካሄደ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዘመናት ተከማችተው የቆዩ ችግሮች በአካታች ሀገራዊ ምክክሩ መፍትሔ በማግኘት ለሕዝቡ እፎይታ ይሰጣሉ የሚል እምነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። በኢኮኖሚው በኩል የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ በክልሎችም ሆነ በሀገር ደረጃ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግረዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከተነሱት ሃሳቦች መካከል የአገልግሎት አሰጣጥን ማፋጠን፣ ሌብነትን ለማጥፋት በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመው፤ ተመራጮች ቃላቸውን ጠብቀው እንዲሠሩ ሕዝቡ አደራ መስጠቱንም ገልጸዋል። በተለይ ቴክኖሎጂን በማስፋፋት በርካታ ሥራዎች እንደሚሠሩና የአገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ በማገዝ የሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ እያገኙ እንደሚሄዱ ነው ያብራሩት። በቀጣይ በርካታ ትላልቅ ሥራዎች እንደሚሰሩ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለአብነትም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከኒውክሌር ኢነርጂ ለማመንጨት እየሰራች ሲሆን ይህም ውጤታማ ይሆናል ብለዋል። ይህ በአፍሪካ ደረጃም ሆነ በኢትዮጵያ ትልቅ ታሪክ መሆኑን ጠቅሰው፤ ታስቦ የሚቀር ሳይሆን የሚፈጸም ሃሳብ በመሆኑ ለመጪው ትውልድ ትልቅ መሠረት ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል። ሕዝባችንን ከመሬትና ከግብርና ተግባሩ መነጠል አይቻልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለግብርና ደግሞ ትልቅ ግብዓት የአፈር ማዳበሪያ ነው ብለዋል። በዚህም ለአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ማሽኖች እየገቡ መሆኑን ጠቁመው የመስኖ ፕሮጀክቶችም በበርካታ ቦታዎች እየተገነቡ እንደሚገኙ አንስተዋል። የመሬት ስፋትን በመጨመርና በክላስተር በማረስ የምርት መጠን ማደጉን ገልጸው ይህንን የበለጠ ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። በመስኖ በጋውን ሙሉና ክረምትም በበቂ ሁኔታ ማምረት ወሳኝ መሆኑን በመጠቆም፤ ይህን ለማድረግ የአፈር ማዳበሪያ በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩንና ይህም ሙሉ ምላሽ ይሰጣል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሀምሳና ስልሳ ዓመታት ተፈጥሮ ጋዝ ለማውጣት ትልቅ ጥረት ብታደርግም ተፈጻሚ ሳይሆን መቆየቱን አስታውሰው፤ አሁን ላይ የመጀመሪያው ምዕራፍ በማውጣት የሁለትና የሦስት ፋብሪካ ግብዓት እየሆነ ይገኛል ብለዋል። በተወሰነ መልኩም የተፈጥሮ ጋዝ እያመረትን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በርካታ ናፍጣ ይጠቀሙ የነበሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ተፈጥሮ ጋዝ እየተቀየሩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ከሁለትና ሶስት ወራት በኋላ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን መጠቀም እንጀምራለን የሚል እምነት እንዳላቸውም ተናግረዋል። ከሁሉም በላይ በቢሾፍቱ እየተገነባ የሚገኘው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። የከተሞች መዘመንና የኮሪደር ልማት ሥራዎች የመጨረሻውና ዋናው ግባቸው ከተማዎችን ዘመናዊ ማድረግ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥን፣ የተሻለ የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን፣ ንጹህ ውሃን፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎትን እንዲሁም በቂ መብራቶችን ማግኘት የሚያካትት ነው ብለዋል። በተጨማሪም ማህበረሰቡ በአቅራቢያው የትምህርትና የጤና አገልግሎት እንዲያገኝ፣ የሥራ ዕድል እንዲፈጠርለትና አዳዲስ ፈጠራዎችን ማሳደግ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ የመፍጠር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ የተጀመረው ከተሞችን የማዘመን ተሞክሮ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከአዲስ አበባ ውጪ በክልሎችም የተሻሉ ከተሞች ይኖሩናል ብለዋል።
ምክክሩ ለኢትዮጵያ ችግሮች ኢትዮጵያዊ መፍትሔ የሚያበጅ ነው- ተመካካሪዎች
Aug 9, 2026 140
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ለሀገሪቱ የረጅም ጊዜ ችግሮች ኢትዮጵያዊ የሆነ ዘላቂ መፍትሔ ማበጀት የሚያስችል ታሪካዊ መድረክ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ 4 ሺህ የሕዝብ ወኪሎችም በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ይህ ሰፊ ተሳትፎን ያረጋገጠ መድረክ የዜጎችን ድምፅ በማሰባሰብ የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ አብሮነት እና የጋራ መግባባት ምሰሶዎች ለማጽናት ታላቅ ተስፋ የተጣለበት ወሳኝ መድረክ ነው። ተመካካሪዎች በግልጽነት መንፈስ የሚያደርጓቸው ጥልቅ ውይይቶች ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ እና ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት እንደሚጥሉ ይታመናል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች እንዳሉት፤ ምክክሩ የጋራ መግባባትን በማጠናከር እና ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ትልቅ ዕድል ፈጥሯል። ከተመካካሪዎች መካከል አባ ገዳ ተሾመ በቀለ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሻግርና በዜጎች መካከል ያለውን ትስስር የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ምክክሩ ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር ሲሆን፣ ይህም ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር ተሰባስበን የምናካሂደው እንደመሆኑ መጠን ልዩ ልዩ ሐሳቦች የሚስተናገዱት በመከባበር እና በመደማመጥ መንፈስ ነው ብለዋል። ይህ በታሪካችን ተደርጎ የማይታወቅ እና የዘገየ ቢሆንም በእኛ ዘመን ለሀገራችን ዘላቂ መፍትሔ ይዞ እንደሚመጣ ትልቅ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ነፃነት ሲሳይ በበኩላቸው፣ እጅግ አሳታፊ በሆነው በዚህ የምክክር መድረክ ሁሉም ተመካካሪዎች በንቃት በመሳተፍ ላይ እንገኛለን ብለዋል። የሐሳብ ልዩነቶች ተፈጥሮአዊ መሆናቸውን በማንሳት አለመግባባቶችን በምክክር መፍታት ለቀጣይ ትውልድ የምትሆን ሀገር ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ለዚህም አሁን እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ዘላቂ ሰላምን እና አብሮነትን ለማረጋገጥ የሚረዳ መልካም አጋጣሚ ነው ብለዋል። ተመካካሪ ዱናሞ ኡሞጎ ሀገራዊ የምክክር መድረኩ በሀገር ሰላምና ልማት ጉዳዮች ላይ በመምከር የተሻለች ሀገር ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል። በምክክሩ ላይ ለኢትዮጵያ ችግሮች እውነተኛ መፍትሔ ለማምጣት የሚያስችሉ ትክክለኛ ሐሳቦችን ማንጸባረቅ የተቻለበት ነው ብለዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም ያሳተፈ በመሆኑ ለሀገሪቱ ተጨባጭ የመፍትሔ ሐሳቦችን የሚያፈልቅ እንደሚሆን ተስፋ እንዳላቸው የተናገሩት ደግሞ ተመካካሪ ተሰማ ላንዴቦ ናቸው። የሀሳብ እና የመናገር ነጻነት በስፋት የሚንጸባረቅበት መድረክ መሆኑንም ገልጸዋል።
የምክክር ጉባኤው በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ትውልድና ሀገር ለመገንባት መሰረት እየጣለ ነው-ተመካካሪዎች
Aug 9, 2026 135
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ትውልድና ሀገር ለመገንባት መሰረት እየጣለ ነው ሲሉ ተመካካሪ አባቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ከተመካካሪዎቹ መካከል አቶ ደረጀ ቦጋለ በሰጡት አስተያየት፤ምክክሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ያካተተና ከአራቱም ማእዘናት የተውጣጡ ብሄር ብሄረሰቦችን ያቀፈ መሆኑን አመልክተው፤ተመካካሪዎች ሀሳባቸውን በነጻነት እየገለጹ ነው ብለዋል። ምክክሩ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ነው፤ ለትውልድ እና ለሀገር የሚበጅ እና ኢትዮጵያን የሚያሻግር መሠረት ለመጣል እየተመካከርን ነው ሲሉም ተናግረዋል። በምክክሩ የችግሮቻችንን ምንጭ በመለየት መፍትሄ የምናስቀምጥበትና እና ታሪክ የምንሰራበት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያውያን ለእኔ ሚለውን ትተን ወደ እኛ ከመጣን ኢትዮጵያ ለሁላችንም ትበቃለች ፤አንድነታችንን ካጠናከርን ኢትዮጰያን ወደ ላቀ ምዕራፍ ማሸጋገር እንችላለን ሲሉም ተናግረዋል። ሌላው የምክክሩ ተሳታፊ አቶ ገበየው ደቦየ በበኩላቸው፤ምክክሩ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግር ለእድገትና ሰላም አስፈላጊ ነው ብለዋል። ምክክሩ የሀገር አንድነትን ለማጠናከር የጎላ አስተዋጽኦ አለው ያሉት አቶ ገበየው፤ ይህም ለኢትዮጵያውያን የተሰጠ ትልቅ እድል መሆኑን ገልጸዋል። በጉባኤው የሚሳተፉ ተመካካሪዎች አደረጃጀት በስፋት ለመሳተፍ የሚያስችልና አካታች መሆኑን ያነሱት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አቶ አበራ ሞናሞ ናቸው። የሀገር አንድነት ጉዳይ ከምንም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን ጠቁመው፤ ምክክሩ ለሀገር እድገትና ዘላቂ ሰላም ጉልህ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-
Aug 9, 2026 134
*ምርጫን በተመለከተ:- ለህዝባችን ቃል እንደገባነው፤አቅማችን በፈቀደ መጠን ምርጫው ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን፤ ህዝቡ በሰላማዊ መንገድ ወጥቶ እንዲመርጥ ለማድረግ እንደ መንግስት ድርሻችንን ተወጥተናል። ህዝቡ የፖለቲካ ሥልጣን በኃይል መያዝ መቆም አለበት ማለት፤ የፖለቲካ ሥልጣን በሰላማዊ መንገድ፤ በምርጫ፤ በህዝብ ተሳታፊነት እንጂ፤ አንድ ቡድን መጥቶ በኃይል መያዝ አይችልም ብሏል የኢትዮጵያ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር በአንድ ድምፅ መልዕክቱን ለእኛም ለሌሎችም አስተላልፏል። በዲሞክራሲያዊ መንገድ መቃወም፤ መሞገት መጠየቅ ነገር ግን የሚሆነኝን መንግስት መምረጥ እችላለሁ ብሏል ሕዝባችን ለዲሞክራሲ ያለው ቁርጠኝነት፤የዲሞክራሲ ሥርዓትን ለመገንባት ያለው ፍላጎት በግልጽ ታይቷል። በሰላማዊ መንገድ መርጫለሁ፤ የመረጥኩት ደግሞ የገባህልኝን ቃል እንደምትፈፅም ስላመንኩ ነው ብሏል 7ኛው ምርጫ በሰላምም፤ በዲሞክራሲያዊ መንገድም በህዝብ ተሳትፎም፤ በፓርቲዎች ተሳትፎም ልዩ ታሪክ ነው። *መደመርን በተመለከተ፦ መደመር በፖለቲካ ማሻሻያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ በማህበራዊ ማሻሻያ ውስጥ ትልቅ ውጤት አምጥቶልናል መደመር ከአስር በላይ በሚሆኑ ቋንቋዎች ተተርጉሟል የመደመር ሀሳብ በተጨባጭ ችግር ፈቺ በተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ያለ እይታ ነው አንድ ሰው የመደመር ሀሳብ ሲያነብ የመደመር ሀሳብ ጥያቄ ሲሆንበት መመርምር ይችላል ይዘቱ ውስጥ ብዙ ታሪክ ብዙ እውቀት አለበት ብዙባህል፣ ብዙ ማንነት እንደያዘ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ይረዳል
መደመር በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ ያመጣ ሀገር በቀል እሳቤ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 9, 2026 151
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ):- የመደመር እሳቤ በሁሉም ዘርፎች ለተመዘገቡ ተጨባጭ ስኬቶች መሰረት የሆነ አገር በቀል እሳቤ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር ባደረጉት ቆይታ የመደመር እሳቤ ከባዕድ የተቀዳ ሳይሆን የሀገር በቀል አስተሳሰብና የፍልስፍና ውጤት መሆኑን ገልጸዋል። በህዝብ ትግል ስም የኦሮሞን ህዝብ ወደ ብሶት ለመክተት ከንቱ ጥረት የሚያደርጉ አካላት መኖራቸውን በማንሳት፤ መደመር በሕዝብ ትግል ስም የሚደረግ የለቅሶ ፖለቲካ ያስቀረ እሳቤ መሆኑንም ጠቁመዋል። እውነተኛ የፖለቲካ መሪ ዋና ተግባር ህዝብን ከገባበት ችግርና መከራ አውጥቶ ወደ በጎና የተሻለ ህይወት ማሸጋገር መሆኑን ነው ያስረዱት። በኢኮኖሚው ዘርፍ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎችን በተመለከተ ባብራሩበት ወቅት፣ በኦሮሚያ ክልል በመስኖ ልማት ትልልቅ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል። ለዚህም በቦረናና በባሌ ዞኖች የተመዘገበው ውጤት ጥሩ ማሳያ መሆኑንም ጠቁመዋል። በቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት ረገድም ትልቅ ስራ መከናወኑን አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመደመር እሳቤ በውጭ ጉዳይ ዘርፍ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ተሰሚነትና ገጽታ ያሳደጉ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በመደመር እሳቤ ዋናው መርህ ወደ ኋላ መመልከት ትምህርት ለመውሰድ ብቻ መሆኑንም ተናግረዋል። የመደመር ሀሳብ የያዘው መጽሐፍ በ10 የተለያዩ ቋንቋዎች መተርጎሙንና ሀሳቡ በተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ማየት መቻሉን ተናግረዋል። በአጠቃላይ የመደመር እሳቤ በሁሉም ዘርፍ የሪፎርም ስራዎች ውስጥ ውጤት እንዲመጣ ወሳኝ ሚና መጫወቱን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫው ስልጣን የሚገኘው በዴሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ መሆኑን አረጋግጧል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 9, 2026 149
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ3/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫው ስልጣን የሚገኘው በዴሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ መሆኑን ለወዳጅም ለጠላትም አረጋግጧል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫው ንቁ ተሳትፍ ማድረጉን ተናግረዋል። በምርጫው የተመዘገበው ከፍተኛ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በአፍሪካ ደረጃም ቢሆን ትልቅና ታሪካዊ ክስተት ተደርጎ የሚወሰድ መሆኑን ተናግረዋል። ይህ ዓይነቱ የህዝብ አመኔታና ድምፅ ደግሞ ከፍተኛ አገራዊ ኃላፊነት የሰጠ መሆኑን አብራርተዋል። ህዝቡ በምርጫው የሰጠው ድምፅ እስካሁን ለተከናወኑት ስራዎች እውቅና የሰጠበት መሆኑን ገልጸው፤ ይህ እውቅና ለቀጣይ ሀገራዊ ሃላፊነቶች ትልቅ የቤት ስራ የሰጠ መሆኑን አመልክተዋል። በምርጫው የኢትዮጵያ ህዝብ ለጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለውን ከፍተኛ ቁርጠኝነት በግልጽ ማሳየቱንም ነው ያነሱት። በምርጫው ታሪክ እንሰራለን ብለን ተናግረን ነበር፣ ህዝባችንም አላሳፈረንም ፤ ታሪክ ሰርቷል ብለዋል። በዚህም ስልጣን የሚገኘው በዴሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ መሆኑን ለወዳጅም ለጠላትም አረጋግጧል ብለዋል። በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበት ትልቅና አሳታፊ ምርጫ ማካሄድ መቻሉ ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሂደት መጠናከር ትልቅ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ሰላምን ለማፅናት በቅንጅት የተሠራው ሥራ ክልሉን ወደ ተሟላ ሰላም እየመለሰው ነው
Aug 8, 2026 296
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰላምን ለማፅናት በቅንጅት የተሠራው ሥራ ክልሉን ወደ ተሟላ ሰላም እየመለሰው መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገለጸ። የክልሉ ፖሊስ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የውይይት መድረክ በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው። በወቅቱም የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጄነራል ዘላለም መንግሥቴ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በክልሉ ሰላምን ለማጽናት በተሻለ ቅንጅት የተሠራው ሥራ ክልሉን ወደ ተሟላ ሰላም እየመለሰው ይገኛል። በሰላም ማስከበር ሥራው ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመተባበር መስዋዕትነት በመክፈል ጭምር የክልሉን ሕዝብ ሰላምና ደኅንነት የማረጋገጥ ሥራ ሠርቷል ብለዋል። ለተገኘው አስተማማኝ ሰላምም ኅብረተሰቡ ከፖሊስ ኃይሉ ጎን በመሆን የጽንፈኛ ኃይሉን ሴራ በማጋለጥና የመረጃ ምንጭ በመሆን ከፍተኛ ድርሻ ማበርከቱን ገልጸዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሪፎርም ሥራ ከመሥራት ባሻገር፣ የክልሉን ሰላምና ደኅንነት በማረጋገጥ ብሎም የተገኘውን ሰላም በማጽናት ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን አብራርተዋል። እንዲሁም ተቋሙን ወደ ዲጂታላይዜሽን በመቀየር፣ በምርመራ፣ ወንጀል በመከላከል፣ በአስተዳደር ልማት ሥራና ሠራተኛን በማገናኘት በኩል ጉልህ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል። ሕዝቡ ከፖሊስ የሚፈልገውን አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ ረገድም የተጠናከረ፣ ያደገና የተለወጠ የፖሊስ ተግባራትን ማከናወን መቻሉን አስረድተዋል። ባለፈው ዓመት የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በማጠናከር በ2019 በጀት ዓመት የፖሊስ ኃይሉ በየትኛውም የግዳጅ ቀጠና የክልሉን ሕዝብ ሰላም የማረጋገጥ ሥራውን የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኮሚሽነሩ አረጋግጠዋል። አሁን የተገኘውን ሰላም ዘላቂነት በማረጋገጥ በኩል ሕዝቡ ከምንጊዜውም በላይ ለፖሊስ እያደረገ ያለውን ትብብርና ድጋፍ የበለጠ እንዲያጠናክርም አሳስበዋል። በመድረኩም በዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና በዕቅድ ትውውቅ በየደረጃው የሚገኙ የፖሊስ አመራሮች እየተሳተፉ ሲሆን መድረኩ ነገም የሚቀጥል ይሆናል።
ምክክሩ መጪው ትውልድ የሰላምና የአብሮነት ተምሳሌት የሆነች ኢትዮጵያን እንዲረከብ መደላድል የሚፈጥር ነው - ተመካካሪ ወጣቶች
Aug 8, 2026 273
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ መጪው ትውልድ የሰላምና የአብሮነት ተምሳሌት የሆነች ኢትዮጵያን እንዲረከብ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ ተወካዮች የተሳተፉበትና በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የሚያተኩረው፣ ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም. የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪ ወጣቶች፤ ምክክሩ አሳታፊና አካታች ከመሆኑም ባሻገር መጪው ትውልድ አንድነቷን የጠበቀችና ሰላሟ የጸና ሀገር እንዲረከብ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት ሊዲያ ዮሴፍ፤ ምክክሩ ሁሉም ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን ያለገደብ የሚያንጸባርቁበት አውድ መፍጠሩን ተናግራለች። ሀገራዊ ምክክሩ ለቆዩ ችግሮችና አለመግባባቶች መንስኤ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በዘላቂነት መፍትሔ ለማግኘት የሚያስችል መደላደል እንደሚፈጥር ያላትን እምነት ገልጻለች። ሌላኛው ተመካካሪ ወጣት እሸቱ ኢረቦ በበኩሉ፤ ምክክሩ ወጣቶች ሰላሟ እና አንድነቷ የጸና ሀገር እንዲረከቡ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ተናግሯል። ምክክሩ በሀገር ግንባታ ሂደት ወጣቶች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ዕድል መፍጠሩን እና ይህም ለሀገር ሰላምና እድገት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስረድቷል። ተመካካሪ ወጣት ገነት አዳኝ፣ የምክክሩ መድረክ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የሰለጠነ የምክክር ባህል መሰረት የሚጣልበት መሆኑን ገልጿል። ሂደቱ መጪው ትውልድ የሰላምና የአብሮነት ተምሳሌት የሆነች ኢትዮጵያን እንዲረከብ የሚያስችል አገራዊ ፋይዳ እንዳለውም ነው የተናገረችው። ተመካካሪ ወጣት ያሲን ሃንፈር የምክክሩ መድረክ ኢትዮጵያውያን ለችግሮቻቸው በአንድ ጣራ ሥር ተሰባስበው በጋራ የሚመክሩበት አውድ መፍጠሩን ገልጿል። ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ ያልነበረ እና አሁን የተገኘ ትልቅ ድል መሆኑን አንስቷል። የበለጸገች ሀገር የመገንባት ሀገራዊ ራዕይ ከግብ እንዲደርስም ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ብሏል። በምክክሩ ሁሉም እኩል ተሳታፊ እንዲሆን መደረጉ ደግሞ ለሀገር ግንባታ ወሳኝ እርምጃ መሆኑንም አብራርቷል።
ፖለቲካ
ብልፅግና ፓርቲ የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ያከናውናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 9, 2026 139
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምፅ ያገኘው ብልፅግና ፓርቲ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እንደሚያከናውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምፅ ያገኘው ብልፅግና ፓርቲ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት በሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ተግባራት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ ድምጽ ያገኘው ብልፅግና ፓርቲ በሚመሰርተው መንግስት በመጪዎቹ አምስት ዓመታት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እንደሚያከናውን ጠቅሰዋል። በሀገር ደረጃ ትልቅ ምክክር እየተካሄደ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዘመናት ተከማችተው የቆዩ ችግሮች በአካታች ሀገራዊ ምክክሩ መፍትሔ በማግኘት ለሕዝቡ እፎይታ ይሰጣሉ የሚል እምነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። በኢኮኖሚው በኩል የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ በክልሎችም ሆነ በሀገር ደረጃ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግረዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከተነሱት ሃሳቦች መካከል የአገልግሎት አሰጣጥን ማፋጠን፣ ሌብነትን ለማጥፋት በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመው፤ ተመራጮች ቃላቸውን ጠብቀው እንዲሠሩ ሕዝቡ አደራ መስጠቱንም ገልጸዋል። በተለይ ቴክኖሎጂን በማስፋፋት በርካታ ሥራዎች እንደሚሠሩና የአገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ በማገዝ የሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ እያገኙ እንደሚሄዱ ነው ያብራሩት። በቀጣይ በርካታ ትላልቅ ሥራዎች እንደሚሰሩ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለአብነትም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከኒውክሌር ኢነርጂ ለማመንጨት እየሰራች ሲሆን ይህም ውጤታማ ይሆናል ብለዋል። ይህ በአፍሪካ ደረጃም ሆነ በኢትዮጵያ ትልቅ ታሪክ መሆኑን ጠቅሰው፤ ታስቦ የሚቀር ሳይሆን የሚፈጸም ሃሳብ በመሆኑ ለመጪው ትውልድ ትልቅ መሠረት ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል። ሕዝባችንን ከመሬትና ከግብርና ተግባሩ መነጠል አይቻልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለግብርና ደግሞ ትልቅ ግብዓት የአፈር ማዳበሪያ ነው ብለዋል። በዚህም ለአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ማሽኖች እየገቡ መሆኑን ጠቁመው የመስኖ ፕሮጀክቶችም በበርካታ ቦታዎች እየተገነቡ እንደሚገኙ አንስተዋል። የመሬት ስፋትን በመጨመርና በክላስተር በማረስ የምርት መጠን ማደጉን ገልጸው ይህንን የበለጠ ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። በመስኖ በጋውን ሙሉና ክረምትም በበቂ ሁኔታ ማምረት ወሳኝ መሆኑን በመጠቆም፤ ይህን ለማድረግ የአፈር ማዳበሪያ በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩንና ይህም ሙሉ ምላሽ ይሰጣል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሀምሳና ስልሳ ዓመታት ተፈጥሮ ጋዝ ለማውጣት ትልቅ ጥረት ብታደርግም ተፈጻሚ ሳይሆን መቆየቱን አስታውሰው፤ አሁን ላይ የመጀመሪያው ምዕራፍ በማውጣት የሁለትና የሦስት ፋብሪካ ግብዓት እየሆነ ይገኛል ብለዋል። በተወሰነ መልኩም የተፈጥሮ ጋዝ እያመረትን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በርካታ ናፍጣ ይጠቀሙ የነበሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ተፈጥሮ ጋዝ እየተቀየሩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ከሁለትና ሶስት ወራት በኋላ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን መጠቀም እንጀምራለን የሚል እምነት እንዳላቸውም ተናግረዋል። ከሁሉም በላይ በቢሾፍቱ እየተገነባ የሚገኘው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። የከተሞች መዘመንና የኮሪደር ልማት ሥራዎች የመጨረሻውና ዋናው ግባቸው ከተማዎችን ዘመናዊ ማድረግ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥን፣ የተሻለ የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን፣ ንጹህ ውሃን፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎትን እንዲሁም በቂ መብራቶችን ማግኘት የሚያካትት ነው ብለዋል። በተጨማሪም ማህበረሰቡ በአቅራቢያው የትምህርትና የጤና አገልግሎት እንዲያገኝ፣ የሥራ ዕድል እንዲፈጠርለትና አዳዲስ ፈጠራዎችን ማሳደግ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ የመፍጠር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ የተጀመረው ከተሞችን የማዘመን ተሞክሮ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከአዲስ አበባ ውጪ በክልሎችም የተሻሉ ከተሞች ይኖሩናል ብለዋል።
ምክክሩ ለኢትዮጵያ ችግሮች ኢትዮጵያዊ መፍትሔ የሚያበጅ ነው- ተመካካሪዎች
Aug 9, 2026 140
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ለሀገሪቱ የረጅም ጊዜ ችግሮች ኢትዮጵያዊ የሆነ ዘላቂ መፍትሔ ማበጀት የሚያስችል ታሪካዊ መድረክ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ 4 ሺህ የሕዝብ ወኪሎችም በስምንት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ይህ ሰፊ ተሳትፎን ያረጋገጠ መድረክ የዜጎችን ድምፅ በማሰባሰብ የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ አብሮነት እና የጋራ መግባባት ምሰሶዎች ለማጽናት ታላቅ ተስፋ የተጣለበት ወሳኝ መድረክ ነው። ተመካካሪዎች በግልጽነት መንፈስ የሚያደርጓቸው ጥልቅ ውይይቶች ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ እና ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት እንደሚጥሉ ይታመናል። ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች እንዳሉት፤ ምክክሩ የጋራ መግባባትን በማጠናከር እና ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ትልቅ ዕድል ፈጥሯል። ከተመካካሪዎች መካከል አባ ገዳ ተሾመ በቀለ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሻግርና በዜጎች መካከል ያለውን ትስስር የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ምክክሩ ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ዕድል የሚፈጥር ሲሆን፣ ይህም ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር መሆኑን አንስተዋል። በኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር ተሰባስበን የምናካሂደው እንደመሆኑ መጠን ልዩ ልዩ ሐሳቦች የሚስተናገዱት በመከባበር እና በመደማመጥ መንፈስ ነው ብለዋል። ይህ በታሪካችን ተደርጎ የማይታወቅ እና የዘገየ ቢሆንም በእኛ ዘመን ለሀገራችን ዘላቂ መፍትሔ ይዞ እንደሚመጣ ትልቅ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል። ሌላኛዋ ተመካካሪ ነፃነት ሲሳይ በበኩላቸው፣ እጅግ አሳታፊ በሆነው በዚህ የምክክር መድረክ ሁሉም ተመካካሪዎች በንቃት በመሳተፍ ላይ እንገኛለን ብለዋል። የሐሳብ ልዩነቶች ተፈጥሮአዊ መሆናቸውን በማንሳት አለመግባባቶችን በምክክር መፍታት ለቀጣይ ትውልድ የምትሆን ሀገር ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ለዚህም አሁን እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ዘላቂ ሰላምን እና አብሮነትን ለማረጋገጥ የሚረዳ መልካም አጋጣሚ ነው ብለዋል። ተመካካሪ ዱናሞ ኡሞጎ ሀገራዊ የምክክር መድረኩ በሀገር ሰላምና ልማት ጉዳዮች ላይ በመምከር የተሻለች ሀገር ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል። በምክክሩ ላይ ለኢትዮጵያ ችግሮች እውነተኛ መፍትሔ ለማምጣት የሚያስችሉ ትክክለኛ ሐሳቦችን ማንጸባረቅ የተቻለበት ነው ብለዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም ያሳተፈ በመሆኑ ለሀገሪቱ ተጨባጭ የመፍትሔ ሐሳቦችን የሚያፈልቅ እንደሚሆን ተስፋ እንዳላቸው የተናገሩት ደግሞ ተመካካሪ ተሰማ ላንዴቦ ናቸው። የሀሳብ እና የመናገር ነጻነት በስፋት የሚንጸባረቅበት መድረክ መሆኑንም ገልጸዋል።
የምክክር ጉባኤው በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ትውልድና ሀገር ለመገንባት መሰረት እየጣለ ነው-ተመካካሪዎች
Aug 9, 2026 135
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦የሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ትውልድና ሀገር ለመገንባት መሰረት እየጣለ ነው ሲሉ ተመካካሪ አባቶች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። ከተመካካሪዎቹ መካከል አቶ ደረጀ ቦጋለ በሰጡት አስተያየት፤ምክክሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ያካተተና ከአራቱም ማእዘናት የተውጣጡ ብሄር ብሄረሰቦችን ያቀፈ መሆኑን አመልክተው፤ተመካካሪዎች ሀሳባቸውን በነጻነት እየገለጹ ነው ብለዋል። ምክክሩ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ነው፤ ለትውልድ እና ለሀገር የሚበጅ እና ኢትዮጵያን የሚያሻግር መሠረት ለመጣል እየተመካከርን ነው ሲሉም ተናግረዋል። በምክክሩ የችግሮቻችንን ምንጭ በመለየት መፍትሄ የምናስቀምጥበትና እና ታሪክ የምንሰራበት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያውያን ለእኔ ሚለውን ትተን ወደ እኛ ከመጣን ኢትዮጵያ ለሁላችንም ትበቃለች ፤አንድነታችንን ካጠናከርን ኢትዮጰያን ወደ ላቀ ምዕራፍ ማሸጋገር እንችላለን ሲሉም ተናግረዋል። ሌላው የምክክሩ ተሳታፊ አቶ ገበየው ደቦየ በበኩላቸው፤ምክክሩ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግር ለእድገትና ሰላም አስፈላጊ ነው ብለዋል። ምክክሩ የሀገር አንድነትን ለማጠናከር የጎላ አስተዋጽኦ አለው ያሉት አቶ ገበየው፤ ይህም ለኢትዮጵያውያን የተሰጠ ትልቅ እድል መሆኑን ገልጸዋል። በጉባኤው የሚሳተፉ ተመካካሪዎች አደረጃጀት በስፋት ለመሳተፍ የሚያስችልና አካታች መሆኑን ያነሱት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አቶ አበራ ሞናሞ ናቸው። የሀገር አንድነት ጉዳይ ከምንም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን ጠቁመው፤ ምክክሩ ለሀገር እድገትና ዘላቂ ሰላም ጉልህ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-
Aug 9, 2026 134
*ምርጫን በተመለከተ:- ለህዝባችን ቃል እንደገባነው፤አቅማችን በፈቀደ መጠን ምርጫው ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን፤ ህዝቡ በሰላማዊ መንገድ ወጥቶ እንዲመርጥ ለማድረግ እንደ መንግስት ድርሻችንን ተወጥተናል። ህዝቡ የፖለቲካ ሥልጣን በኃይል መያዝ መቆም አለበት ማለት፤ የፖለቲካ ሥልጣን በሰላማዊ መንገድ፤ በምርጫ፤ በህዝብ ተሳታፊነት እንጂ፤ አንድ ቡድን መጥቶ በኃይል መያዝ አይችልም ብሏል የኢትዮጵያ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር በአንድ ድምፅ መልዕክቱን ለእኛም ለሌሎችም አስተላልፏል። በዲሞክራሲያዊ መንገድ መቃወም፤ መሞገት መጠየቅ ነገር ግን የሚሆነኝን መንግስት መምረጥ እችላለሁ ብሏል ሕዝባችን ለዲሞክራሲ ያለው ቁርጠኝነት፤የዲሞክራሲ ሥርዓትን ለመገንባት ያለው ፍላጎት በግልጽ ታይቷል። በሰላማዊ መንገድ መርጫለሁ፤ የመረጥኩት ደግሞ የገባህልኝን ቃል እንደምትፈፅም ስላመንኩ ነው ብሏል 7ኛው ምርጫ በሰላምም፤ በዲሞክራሲያዊ መንገድም በህዝብ ተሳትፎም፤ በፓርቲዎች ተሳትፎም ልዩ ታሪክ ነው። *መደመርን በተመለከተ፦ መደመር በፖለቲካ ማሻሻያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ በማህበራዊ ማሻሻያ ውስጥ ትልቅ ውጤት አምጥቶልናል መደመር ከአስር በላይ በሚሆኑ ቋንቋዎች ተተርጉሟል የመደመር ሀሳብ በተጨባጭ ችግር ፈቺ በተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ያለ እይታ ነው አንድ ሰው የመደመር ሀሳብ ሲያነብ የመደመር ሀሳብ ጥያቄ ሲሆንበት መመርምር ይችላል ይዘቱ ውስጥ ብዙ ታሪክ ብዙ እውቀት አለበት ብዙባህል፣ ብዙ ማንነት እንደያዘ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ይረዳል
መደመር በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ ያመጣ ሀገር በቀል እሳቤ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 9, 2026 151
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ):- የመደመር እሳቤ በሁሉም ዘርፎች ለተመዘገቡ ተጨባጭ ስኬቶች መሰረት የሆነ አገር በቀል እሳቤ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር ባደረጉት ቆይታ የመደመር እሳቤ ከባዕድ የተቀዳ ሳይሆን የሀገር በቀል አስተሳሰብና የፍልስፍና ውጤት መሆኑን ገልጸዋል። በህዝብ ትግል ስም የኦሮሞን ህዝብ ወደ ብሶት ለመክተት ከንቱ ጥረት የሚያደርጉ አካላት መኖራቸውን በማንሳት፤ መደመር በሕዝብ ትግል ስም የሚደረግ የለቅሶ ፖለቲካ ያስቀረ እሳቤ መሆኑንም ጠቁመዋል። እውነተኛ የፖለቲካ መሪ ዋና ተግባር ህዝብን ከገባበት ችግርና መከራ አውጥቶ ወደ በጎና የተሻለ ህይወት ማሸጋገር መሆኑን ነው ያስረዱት። በኢኮኖሚው ዘርፍ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎችን በተመለከተ ባብራሩበት ወቅት፣ በኦሮሚያ ክልል በመስኖ ልማት ትልልቅ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል። ለዚህም በቦረናና በባሌ ዞኖች የተመዘገበው ውጤት ጥሩ ማሳያ መሆኑንም ጠቁመዋል። በቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት ረገድም ትልቅ ስራ መከናወኑን አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመደመር እሳቤ በውጭ ጉዳይ ዘርፍ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ተሰሚነትና ገጽታ ያሳደጉ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በመደመር እሳቤ ዋናው መርህ ወደ ኋላ መመልከት ትምህርት ለመውሰድ ብቻ መሆኑንም ተናግረዋል። የመደመር ሀሳብ የያዘው መጽሐፍ በ10 የተለያዩ ቋንቋዎች መተርጎሙንና ሀሳቡ በተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ማየት መቻሉን ተናግረዋል። በአጠቃላይ የመደመር እሳቤ በሁሉም ዘርፍ የሪፎርም ስራዎች ውስጥ ውጤት እንዲመጣ ወሳኝ ሚና መጫወቱን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫው ስልጣን የሚገኘው በዴሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ መሆኑን አረጋግጧል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Aug 9, 2026 149
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ3/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫው ስልጣን የሚገኘው በዴሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ መሆኑን ለወዳጅም ለጠላትም አረጋግጧል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫው ንቁ ተሳትፍ ማድረጉን ተናግረዋል። በምርጫው የተመዘገበው ከፍተኛ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በአፍሪካ ደረጃም ቢሆን ትልቅና ታሪካዊ ክስተት ተደርጎ የሚወሰድ መሆኑን ተናግረዋል። ይህ ዓይነቱ የህዝብ አመኔታና ድምፅ ደግሞ ከፍተኛ አገራዊ ኃላፊነት የሰጠ መሆኑን አብራርተዋል። ህዝቡ በምርጫው የሰጠው ድምፅ እስካሁን ለተከናወኑት ስራዎች እውቅና የሰጠበት መሆኑን ገልጸው፤ ይህ እውቅና ለቀጣይ ሀገራዊ ሃላፊነቶች ትልቅ የቤት ስራ የሰጠ መሆኑን አመልክተዋል። በምርጫው የኢትዮጵያ ህዝብ ለጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለውን ከፍተኛ ቁርጠኝነት በግልጽ ማሳየቱንም ነው ያነሱት። በምርጫው ታሪክ እንሰራለን ብለን ተናግረን ነበር፣ ህዝባችንም አላሳፈረንም ፤ ታሪክ ሰርቷል ብለዋል። በዚህም ስልጣን የሚገኘው በዴሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ መሆኑን ለወዳጅም ለጠላትም አረጋግጧል ብለዋል። በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበት ትልቅና አሳታፊ ምርጫ ማካሄድ መቻሉ ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሂደት መጠናከር ትልቅ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ሰላምን ለማፅናት በቅንጅት የተሠራው ሥራ ክልሉን ወደ ተሟላ ሰላም እየመለሰው ነው
Aug 8, 2026 296
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰላምን ለማፅናት በቅንጅት የተሠራው ሥራ ክልሉን ወደ ተሟላ ሰላም እየመለሰው መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገለጸ። የክልሉ ፖሊስ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የውይይት መድረክ በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው። በወቅቱም የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጄነራል ዘላለም መንግሥቴ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በክልሉ ሰላምን ለማጽናት በተሻለ ቅንጅት የተሠራው ሥራ ክልሉን ወደ ተሟላ ሰላም እየመለሰው ይገኛል። በሰላም ማስከበር ሥራው ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመተባበር መስዋዕትነት በመክፈል ጭምር የክልሉን ሕዝብ ሰላምና ደኅንነት የማረጋገጥ ሥራ ሠርቷል ብለዋል። ለተገኘው አስተማማኝ ሰላምም ኅብረተሰቡ ከፖሊስ ኃይሉ ጎን በመሆን የጽንፈኛ ኃይሉን ሴራ በማጋለጥና የመረጃ ምንጭ በመሆን ከፍተኛ ድርሻ ማበርከቱን ገልጸዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሪፎርም ሥራ ከመሥራት ባሻገር፣ የክልሉን ሰላምና ደኅንነት በማረጋገጥ ብሎም የተገኘውን ሰላም በማጽናት ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን አብራርተዋል። እንዲሁም ተቋሙን ወደ ዲጂታላይዜሽን በመቀየር፣ በምርመራ፣ ወንጀል በመከላከል፣ በአስተዳደር ልማት ሥራና ሠራተኛን በማገናኘት በኩል ጉልህ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል። ሕዝቡ ከፖሊስ የሚፈልገውን አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ ረገድም የተጠናከረ፣ ያደገና የተለወጠ የፖሊስ ተግባራትን ማከናወን መቻሉን አስረድተዋል። ባለፈው ዓመት የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በማጠናከር በ2019 በጀት ዓመት የፖሊስ ኃይሉ በየትኛውም የግዳጅ ቀጠና የክልሉን ሕዝብ ሰላም የማረጋገጥ ሥራውን የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኮሚሽነሩ አረጋግጠዋል። አሁን የተገኘውን ሰላም ዘላቂነት በማረጋገጥ በኩል ሕዝቡ ከምንጊዜውም በላይ ለፖሊስ እያደረገ ያለውን ትብብርና ድጋፍ የበለጠ እንዲያጠናክርም አሳስበዋል። በመድረኩም በዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና በዕቅድ ትውውቅ በየደረጃው የሚገኙ የፖሊስ አመራሮች እየተሳተፉ ሲሆን መድረኩ ነገም የሚቀጥል ይሆናል።
ምክክሩ መጪው ትውልድ የሰላምና የአብሮነት ተምሳሌት የሆነች ኢትዮጵያን እንዲረከብ መደላድል የሚፈጥር ነው - ተመካካሪ ወጣቶች
Aug 8, 2026 273
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ መጪው ትውልድ የሰላምና የአብሮነት ተምሳሌት የሆነች ኢትዮጵያን እንዲረከብ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ተመካካሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ ተወካዮች የተሳተፉበትና በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የሚያተኩረው፣ ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም. የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪ ወጣቶች፤ ምክክሩ አሳታፊና አካታች ከመሆኑም ባሻገር መጪው ትውልድ አንድነቷን የጠበቀችና ሰላሟ የጸና ሀገር እንዲረከብ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። ከተመካካሪዎቹ መካከል ወጣት ሊዲያ ዮሴፍ፤ ምክክሩ ሁሉም ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን ያለገደብ የሚያንጸባርቁበት አውድ መፍጠሩን ተናግራለች። ሀገራዊ ምክክሩ ለቆዩ ችግሮችና አለመግባባቶች መንስኤ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በዘላቂነት መፍትሔ ለማግኘት የሚያስችል መደላደል እንደሚፈጥር ያላትን እምነት ገልጻለች። ሌላኛው ተመካካሪ ወጣት እሸቱ ኢረቦ በበኩሉ፤ ምክክሩ ወጣቶች ሰላሟ እና አንድነቷ የጸና ሀገር እንዲረከቡ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ተናግሯል። ምክክሩ በሀገር ግንባታ ሂደት ወጣቶች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ዕድል መፍጠሩን እና ይህም ለሀገር ሰላምና እድገት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስረድቷል። ተመካካሪ ወጣት ገነት አዳኝ፣ የምክክሩ መድረክ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የሰለጠነ የምክክር ባህል መሰረት የሚጣልበት መሆኑን ገልጿል። ሂደቱ መጪው ትውልድ የሰላምና የአብሮነት ተምሳሌት የሆነች ኢትዮጵያን እንዲረከብ የሚያስችል አገራዊ ፋይዳ እንዳለውም ነው የተናገረችው። ተመካካሪ ወጣት ያሲን ሃንፈር የምክክሩ መድረክ ኢትዮጵያውያን ለችግሮቻቸው በአንድ ጣራ ሥር ተሰባስበው በጋራ የሚመክሩበት አውድ መፍጠሩን ገልጿል። ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ ያልነበረ እና አሁን የተገኘ ትልቅ ድል መሆኑን አንስቷል። የበለጸገች ሀገር የመገንባት ሀገራዊ ራዕይ ከግብ እንዲደርስም ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ብሏል። በምክክሩ ሁሉም እኩል ተሳታፊ እንዲሆን መደረጉ ደግሞ ለሀገር ግንባታ ወሳኝ እርምጃ መሆኑንም አብራርቷል።
ማህበራዊ
በአፋር ክልል የጠቅላይ ፍርድ ቤት አሰራሮችን በማቀላጠፍ የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ ተችሏል
Aug 9, 2026 32
ሰመራ፣ ነሀሴ 3/2018 (ኢዜአ)፡-በአፋር ክልል የጠቅላይ ፍርድ ቤት አሰራሮችን በማቀላጠፍ የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሙሳ አብዶ ገለጹ። የአፋር ክልል ምክር ቤት 6ኛ የምርጫ ዘመን፣ 5ኛ የሥራ ዘመን፣ 10ኛ መደበኛ ጉባዔውን በማካሄድ ላይ ነው። በዛሬ ሁለተኛ ቀን ውሎው የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሪፖርት ፕሬዚዳንቱ ሙሳ አብዶ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ዲጂታላይዜሽን አሰራርን በመተግበር የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ ተችሏል። ይህም በፍርድ ቤቶች የነበረውን የሥራ ጫና ማስቀረቱን ተናግረው፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለአቤቱታ ከቀረቡ 14 ሺህ 309 መዝገቦች ውስጥ ከ13 ሺህ በላይ መዝገቦች ውሳኔ አግኝተዋል ብለዋል። በእዚህም አፈጻጸሙ 97 ከመቶ መሆኑን የገለፁት አቶ ሙሳ፣ ካለፈው ዓመት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የሦስት ከመቶ ብልጫ አለው ብለዋል። ለውጤታማነቱም ተከታታይነት ያላቸው የክትትልና የድጋፍ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። በፍርድ ቤቶች የሚሰጡ አገልግሎቶች ጥራትና ፍጥነት እንዲኖራቸው አሰራርን ከማዘመን ባለፈ የሰው ሀይሉን ለማብቃት መሰራቱንም ፕሬዚዳንቱ አመልክተዋል።
የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የከተማዋ የብልፅግና ጉዞ ዋና ማዕከል ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Aug 9, 2026 109
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ):- የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የከተማዋ የብልፅግና ጉዞ ዋና ማዕከል መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ "ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል" በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን የአምስተኛ ዙር ሰልጣኞች አስመርቋል፡፡ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የከተማው ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ቡዜና አልከድር፣ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባደረጉት ንግግር፤ የማዕከሉ ተመራቂዎች የመቻል ህያው ምስክር መሆናቸውን ገልጸዋል። ሰልጣኞቹ ቀደም ሲል መስራት እየፈለጉ ያልቻሉበትን፣ የመገፋትና የጥላቻ ህይወት ያስተናገዱበትን ጊዜ አሳልፈው ዛሬ ላይ ሕይወታቸው ታድሶ፣ በፍቅር ታንጸውና በተስፋ ተሞልተው የብርሃን ወጋገን ማየት መቻላቸውን ተናግረዋል። ሰልጣኞቹ በማዕከሉ በቆዩበት ጊዜ የስራ ባለቤት የሚሆኑበትንና ለሌሎችም የሚተርፉበትን አቅምና ክህሎት ማግኘታቸውን በመግለጽ፣ ነገ ደግሞ ከዚህ የበለጠ ዕድልና ስኬት እንደሚጠብቃቸው ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ውጤቱ እየጨመረ በመምጣቱ ከሀገር አልፎ ለሌሎችም ተምሳሌት እንሆናለን ብለዋል፡፡ ከተማዋንና ሀገርን ለማበልፀግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የሰው ልጅ ዋና ማዕከል መሆኑንና የብልፅግናም ዋና ግብ የሕብረተሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ አብራርተዋል። የለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ሂርጳሳ ጫላ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ የሚሹ ሴቶች የተሃድሶና የሙያ ስልጠና እንዲያገኙ ማድረጉን ጠቁመዋል። በዚህም በአምስተኛው ዙር ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ 858 ሰልጣኞች ለምረቃ መብቃታቸውን ተናግረዋል። ሰልጣኞቹ የንድፈ-ሃሳብና የክህሎት ስልጠና አጠናቀው በወሰዱት የሙያ ብቃት ምዘና 95 በመቶ ያህሉ ማለፋቸውን አስረድተዋል። ማዕከሉ ባለፉት አራት ዙሮች የሰለጠኑትን ጨምሮ እስካሁን በአጠቃላይ 3 ሺህ 259 ሴቶችን በተሃድሶና በሙያ ስልጠና ማብቃት መቻሉንም ገልጸዋል። የኢፌዴሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ተቋሙ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች እና መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 898 ተማሪዎች አስመርቋል ብለዋል። የትምህርት እና የሥልጠና ጥራትን ለማሳደግ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመው፤ አዳዲስ መደበኛ እና አጫጭር የሥልጠና ፕሮግራሞች ተቀርጸው ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልጸዋል። ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር የጋራ ፕሮግራሞችን የማስተሳሰር ሥራ መሠራቱንም ዋና ዳይሬክተሩ አመልክተዋል። የልምድ፣ የክህሎት፣ የዕውቀት፣ የቴክኖሎጂ ኢንኩቤሽን እንዲሁም ከታዳጊነት ዕድሜ ጀምሮ የሙያ ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰዋል። ከግሉ ዘርፍ ጋር በመተባበርም በፋሽን ኢንዱስትሪና በሌሎች ዘርፎች ሥልጠናዎች እየተሰጡ እንደሚገኙም አስታውቀዋል። ከመደበኛ ተመራቂዎች መካከል አስናቀች ወንድሙ እንደተናገረችው፤ ከመንግስት ስራ ባሻገር የራሷን ስራ ፈጥራ ሀገሯንና ወገኗን ለማገልገል ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች። ሌላኛዋ የማዕረግ ተመራቂ ብዙዬ ዝናቡ በበኩሏ፤ በትምህርት ቆይታቸው ከንድፈ-ሀሳብ ባሻገር ሰፊ የተግባር ትምህርት ማግኘታቸውን በመጥቀስ፣ በሙያዋ ሀገሯን ለማገልገል ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች። ከደቡብ ሱዳን መጥታ ትምህርቷን የተከታተለችው ሰልጣኝ ረቢካ ኤንግል የኢትዮጵያ መንግስት የትምህርት እድል ስለሰጣት ምስጋናዋን አቅርባለች። አክላም በቆይታዋ ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር የኢትዮጵያን ብዙ ባህሎችና ወጎች ማወቅና መገንዘብ እንደቻለች ተናግራለች።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል የስብዕና ግንባታ ሰልጣኞችን አስመረቁ
Aug 9, 2026 115
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተለያየ ማህበራዊ ችግር ውስጥ የነበሩ በለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል በ5ኛ ዙር የክህሎት እና የስብዕና ግንባታ የሰለጠኑ 858 ሰልጣኞችን አስመረቁ። ከንቲባ አዳነች፥በከተማችን ከምንሰራቸው ሰው ተኮር ስራዎች አንዱ ትላንት በጎዳና፣ በችግር እና በተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶች ውስጥ የነበሩ ሴቶችን በሙያ ክህሎትና ስብዕና ገንብተን ከነበሩበት አስከፊ ህይወት በማውጣት ወደ ተሻለ ህይወት የምናሰማራበት ቀዳሚው ተግባር ነው ብለዋል። አዲስ አበባችን ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት እንዲሁም ለዘመናት የከረሙ ስብራቶቿ የሚጠገኑባት ከተማ የማድረግ የተግባር ውጤት ፍሬ ማሳያዎች ከለነገዋ ተመርቀው አዲስ ህይወት እየመሩ ያሉት ሴቶች እህቶቻችን ናቸው ሲሉ ጠቁመዋል። የዛሬዎቹ ተመራቂዎችን ጨምሮ በማዕከሉ በድምሩ 3259 ሰልጣኞችን አስመርቀን ወደ ስራው ዓለም እንዲቀላቀሉ በማድረግ ህይወታቸውን በተሻለ መንገድ እንዲመሩና ለሌሎችም አርዓያ እንዲሆኑ አድርገናል። አክለውም፥ውድ ተመራቂዎች አስከፊውን ትላንታችሁን አልፋችሁ፤በማዕከሉ በነበራችሁ ቆይታ በቀሰማችሁት ክህሎት እና ባገኛችሁት የተሀድሶ ስልጠና ዛሬ ማሸነፍ ችላችኋል ነው ያሉት። ነገም በስራው ዓለም ስኬታማ ለመሆን የሚገጥማቸውን ማንኛውንም ፈተና በማሸነፍ ህይወታችሁን ይበልጥ ብሩህ እንደሚያደርጉ ከንቲባዋ እምነታቸውን በመግለጽ የእንኳን ደስ አላቹ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የበጎ ፈቃድ ደም ልገሳ በተለያየ ምክንያት የደም እጥረት የሚያጋጥማቸውን ወገኖች ችግር ለመፍታት እያገዘ ነው
Aug 9, 2026 102
ድሬዳዋ፣ ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ):-የበጎ ፈቃድ ደም ልገሳ በተለያየ ምክንያት የደም እጥረት የሚያጋጥማቸውን ወገኖች ችግር ለመፍታት እያገዘ መሆኑን በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የደም ባንክ አገልግሎት ገለፀ። በድሬዳዋ አስተዳደር በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተከናወኑ ካሉ 14 የልማት ዘርፎች መካከል የደም ልገሳ፣ የበሽታ መከላከል ትምህርት እና ነፃ የሕክምና አገልግሎት ተጠቃሾች ናቸው። በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የደም ባንክ አገልግሎት አስተባባሪ ፋሲል ዘውዴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በበጋና በክረምት ባህል እየሆነ በመጣው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚሰበሰበው ደም ዕጥረትን በማቃለል መሰረታዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። በተያዘው የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትም የህብረተሰቡን የደም ልገሳ ባህል በማጠናከር አስካሁን ድረስ ከ745 ከረጢት ደም በላይ መሰብሰቡን ጠቅሰዋል። ይሄ በጎ ተግባር በወሊድ ወቅት እና በድንገተኛ አደጋ ደም የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች ችግር በመፍታት ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር የራሱን እገዛ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። በበጎ ፈቃድ ደም የለገሱ የመንግስት ሠራተኞችና ወጣቶች በበኩላቸው፤ የሚለግሱት ደም በደም ዕጥረት አንድም ሰው እንዳይሞት ስለሚያደርግ በተግባሩ መሳተፋቸውን ተናግረዋል። ወይዘሮ አረጋሽ ንጉስ የለገሱት ደም ወላድ እናትን የሚታደግና ሕይወትን የሚያለመልም በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ጤናማ ሰው በየሦስት ወራት ደም መለገስ እንደሚችል ባገኘሁት ግንዛቤ መሠረት በፍቃደኝነት ደም ለግሺያለሁ ያለው ደግሞ ወጣት አፈንዲ መሐመድ ነው። በተለያዩ አደጋዎች ተጎድተው በሕክምና ተቋማት ተኝተው ደም ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ደራሽ መሆን መንፈሳዊ እርካታ የሚሰጥ መልካም ተግባር መሆኑን ተናግሯል።
ኢኮኖሚ
ቀልጣፋ የአሰራር ስርዓት በመተግበር አልሚዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለመሳብ ተችሏል
Aug 9, 2026 98
ጋምቤላ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦ሀገሪቱ ያሏትን የኢንቨስትመንት እድሎች ለባለሀብቶች የማስተዋወቅ እና አገልግሎቶችን ቀልጣፋ የሚያደርጉ አሰራሮችን በመተግበር በርካታ አልሚዎችን ወደ ሀገር ውስጥ መሳብ መቻሉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለጸ። የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈፃሚ አካላት በጋምቤላ ከተማ እያካሄዱት ባለው የጋራ ምክክር በ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምና በአዲሱ በጀት ዓመት እቅድ በመምከር የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዳጋቶ ኩምቤ በመድረኩ ላይ እንዳሉት የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ አልሚዎችን ለመሳብ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስገኙ ነው። በዚህም በበጀት ዓመቱ ብቻ 528 የውጪ ሀገር ባለሃብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ''ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ 2026 ፎረም’’ የኢንቨስትመንት ስምምነትንም የፈረሙ ሰባት ተቋማት 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ካፒታል ፈሰስ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣይም የዲጂታል አገልግሎቱን በማስፋትና ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጠናከርና የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ተመራጭነት ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የኮሚሽኑ የስፔሻል ኢኮኖሚ ዞን ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ዝናቡ ይርጋ በበኩላቸው፥ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ወደ ውጤት በመቀየር የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራሩ ይጠናከራል ብለዋል። ለዚህም የመሰረተ ልማት አውታሮችን ተደራሽነት የማስፋትና የአሰራር ማእቀፎችን ማስፋት ላይ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የሚተገበር መሆኑን ተናግረዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፥ ባለሃብቶች ለሚያጋጥማቸው ተግዳሮቶች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ቅንጅታዊ አሰራሮችን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። የምክክር መድረኩ በ2018 እቅድ አፈፃፀምና በአዲሱ በጀት ዓመት ውይይት በማድረግ የትኩረት አቅጣጫ ያስቀመጠ ሲሆን ተሳፊዎች በዛሬው ዕለት ከጋምቤላ ክልል ርዕሰ መሰተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ጋር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። በቀጣይም የልማት ምልከታ የመስክ ጉብኝት በማካሄድ መርሃ ግብራቸውን እንደሚያጠናቅቁ ይጠበቃል።
በጉጂ ዞን በምርት ዘመኑ ከ231 ሺህ ኩንታል በላይ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ ቀረበ
Aug 9, 2026 209
አዶላ፤ ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በዘንድሮው የምርት ዘመን ከ231 ሺህ ኩንታል በላይ የተፈጥሮ ጣእምና ጥራቱን የጠበቀ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ መቅረቡን የዞኑ ንግድ ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡ የጉጂ ዞን በኢትዮጵያ ከሚገኙ የቡና አምራች አካባቢዎች መካከል በጥራትና በምርት መጠን በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ አካባቢ ነው፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ዋጋ ከሚሸጡ የታጠቡና ያልታጠቡ የቡና አይነቶች መካከል የጉጂ ቡና ይጠቀሳል፡፡ በዞኑ የሚገኙ አነስተኛ አባወራ አምራቾች፣ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራትና ባለሀብቶች በቡና መልቀም፣ ማጠብና ማድረቅ ሂደት ላይ ባላቸው ልምድ ምክንያት የምርቱን ጥራት ለማስጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዞኑ የተደረጉ የጥራት ቁጥጥር ስራዎች፣ የኮንትሮባንድ ንግድን የመግታት እርምጃዎችና አምራቾችን በቀጥታ ከማዕከላዊ ገበያ ጋር የማገናኘት አሰራር ምርቱ በጥራትና በስፋት ለገበያ እንዲቀርብ አግዟል፡፡ በዞኑ ንግድ ጽህፈት ቤት የእቅድና በጀት ባለሙያ አቶ ደረሰ ደንቆ በ2018 በጀት አመት ከዞኑ በጥራትና በብዛት የሚወዳደር የቡና ምርት ለማቅረብ የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን አስታውሰዋል፡፡ በእስካሁኑ ክንውንም ከዞኑ ቡና አምራች ወረዳዎች የተሰበሰበ 231 ሺህ 190 ኩንታል የተፈጥሮ ጣእምና ጥራት ያለው ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል ብለዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ 174 ሺህ 100 ደረቅ እና 57 ሺህ 90 ኩንታል ታጥቦ የተቀሸረ የደረቅ ቡና ምርት እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ በዞኑ የተቋቋሙ በርካታ የደረቅና የእሼት ቡና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ቡናን በብዛትና በጥራት እያዘጋጁ በማቅረብ ላይ እንደሆኑም ጠቁመዋል፡፡ የጉጂ ቡና በጣእምና ጥራቱ ተመራጭና ተፈላጊ እየሆነ በመምጣቱ ከተለያዩ ቡና ላኪ ኩባንያዎች እውቅናና የምስክር ወረቀት መሰጠቱንም አስታውሰዋል፡፡ እውቅናው የዞኑ የተፈጥሮ ቡና ጣእምና ጥራቱን ሳይለቅ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ መነሳሳት መፍጠሩንም ገልጸዋል፡፡ የዞኑ የቡና ልማት የሚከናወነው በተፈጥሮ ደኖች ጥላ ስር በመሆኑ ባለልዩ የተፈጥሮ ጣእም ባለቤት እንዲሆን ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ በዞኑ አዶላ ከተማ የተቋቋመው የቡና ጣእምና ቅምሻ ማእከል ለምርት ጥራትና አቅርቦት መሻሻል መነሳሳት ፈጥሯል ብለዋል፡፡ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ደስታ ገብረየሱስ በበኩላቸው መንግስት ለቡና ልማት የሰጠው ትኩረት ምርታማነትን በተሻለ እያሳደገ ነው ብለዋል፡፡ በዞኑ 13 ወረዳዎች በቡና ልማት ከተሸፈነው ከ187 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት አብዛኛው በተሻሻለ የቡና ተክል የለማ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በዞኑ ከሰብል ልማትና ከእንስሳት እርባታ ጎን ለጎን ከ110 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በቡና ልማት መሳተፋቸውንም አስታውቀዋል፡፡ በዞኑ አዶላ ወረዳ አንፈራራ ቀበሌ በቡና ልማት የተሳተፉት አቶ ገመዳ ሀለኬ ለልማቱ ትኩረት መሰጠቱ ምርታችንን በማሳደግ ተጠቃሚ አድርጎናል ብለዋል፡፡ ነባሩን የቡና ልማት በተሻሻለ ዝርያ በመተካት ብዛትና ጥራት ያለው ምርት በመሰብሰብ ለገበያ እያቀረቡ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የተሻሻለው የቡና ዝርያ ምርታማነትን ከማሳደግ ሌላ ብርድና በሽታ በመቋቋም የተሻለ መርት የሚሰጥ መሆኑም እንዲሁ።
በአፋር ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Aug 8, 2026 400
ሰመራ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦ በአፋር ክልል የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ ገለጹ። የአፋር ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ የሥራ ዘመን፣ 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል። ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ የክልሉን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ ናቸው። በተለይም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን የተቻለ ሲሆን፤ በመስኖ ልማትም 142 ሺህ 675 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎችና አትክልቶች መሸፈን መቻሉን ተናግረዋል። በዚህም መሠረት በበጀት ዓመቱ ከ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት የተለያዩ የግብርና ግብዓቶች መሰራጨታቸውን አመልክተው፤ ከዚህ ውስጥም ከ47 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ መደረጉን ገልጸዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በክልሉ ያልለሙ መሬቶችን ወደ እርሻ ሥራ በማስገባት የአርብቶ አደሩና ከፊል አርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ማስቻሉንም ነው ያብራሩት። በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን በማስወገድ በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ16 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም አስረድተዋል። የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን እስከ ታች ድረስ በማውረድና የንቅናቄ ሥራዎችን በማከናወን ከ405 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል በሪፖርታቸው፤ በክልል ደረጃ 80 ሺህ 621 ዜጎች የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸውንም ነው ለምክር ቤቱ የገለጹት።
በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው
Aug 8, 2026 376
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸው ተገለጸ። የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸሙን ገምግሟል። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ የመንግሥት ረዳት ተጠሪ አቶ አሸናፊ ኤልያስ እንዳሉት፣ የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው። ከተማን ከወረዳና ከገጠር ቀበሌዎች የሚያገናኙ መንገዶችንና የአገልግሎት መስጫ ተቋማትን ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት መሰራቱን ጠቁመዋል። የክልሉ ከተሞች ለኑሮ፣ ለሥራና ለኢንቨስትመንት ምቹ እንዲሆኑ የኮሪደር ልማት ስራን በመስራት፣ የመኖሪያና የኢንቨስትመንት ቦታ በማቅረብ የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በከተሞችና በገጠር መካከል ያለውን የእድገትና የልማት ልዩነት ለማጥበብ በገጠር ኮሪደርና ሞዴል መንደሮችን የማስፋፋት ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ አሸናፊ ተናግረዋል። የሲዳማ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ሰለሞን በበኩላቸው፣ የክልሉ ከተሞች ደረጃውን በጠበቀ ፕላን እንዲመሩ ለማድረግ በተከናወነው ሥራ የ73 ከተሞች የፕላን ክለሳና አዲስ ፕላን የማዘጋጀት ሥራ መሰራቱን ጠቁመዋል። በከተሞች የአገልግሎት አሰጣጡን ከማሻሻል አኳያ በሐዋሳ በክልሉና በከተማ አስተዳደሩ «መሶብ» የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን ወደ ስራ በማስገባት ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት መቻላቸውን ገልጸዋል። ይህን ለማስፋት በስድስት ከተሞች የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ግንባታ ተጠናቆ የቁሳቁስ የማሟላት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ በተያዘው የ2019 በጀት ዓመት ወደ ሥራ እንዲገቡ ይደረጋል ብለዋል። የወንዶገነት ወረዳ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ መልካሙ ኤርሚያስ እንዳሉት፣ በወረዳው በከተማና በገጠር መካከል ያለውን የልማት ልዩነት ለማመጣጠን እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በወረዳው የገጠር ኮሪደር ልማትና ሞዴል የገጠር መንደሮችን በማስፋፋት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተከናወነ ተግባር 13 ሞዴል ቤቶችን መገንባት እንደተቻለ ገልጸዋል። ወንዶገነት በወሻ ከተማ አቅራቢያ ያሉ የተፈጥሮ ፍልውኃዎችን በአግባቡ አልምቶ የቱሪስት ፍሰቱንና ገቢን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የሴክተሩ የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ የክልሉ አራት ዞኖች ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ፣ የወረዳ አመራሮችና የሴክተሩ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አዲስ አበባ የ"ስማርት ሲቲ" ግንባታ ልምዷን ለቤኒን ሪፐብሊክ አካፍላለች
Aug 7, 2026 197
አዲስ አበባ፤ነሃሴ 1/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቤኒን ሪፐብሊክ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንና ኢኖቬሽን እና ፈጠራ ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን ለተመራ የልዑክ ቡድን አዲስ አበባ እየተገበረች ያለውን ስማርት ሲቲ ግንባታ ጋር በተያያዘ ልምድ አካፍለዋል። ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ቤኒን የጀመረችውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማሳካት በከተማችን ተግብረነው ውጤታማ እየሆነ ያለውን Smart City (ስሉጥ ከተማ) ግንባታን በተመለከት ልምድ ማካፈላቸውን ገልጸዋል። በተለይም በዋና ዋና ግቦች (Smart Economy, Smart Environment, Smart Governance, Smart Living, Smart Mobility, Smart People) እና ለስኬቶቻችን መሰረት የሆኑት የተቋማት ቅንጅት፣ የህጎችና ደንቦች ትግበራ፣ የሕዝብ ተሳትፎ፣ የመንግሥትና የግል ዘርፍ ቅንጅታዊ ሥራዎችን ለልዑክ ቡድኑ አካፍለናል ነው ያሉት።
የቁልፍ መሰረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት አዋጅ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም መከበር ጉልህ ሚና ይኖረዋል
Aug 7, 2026 204
አዲስ አበባ፤ ነሃሴ 1/2018 (ኢዜአ)፦የቁልፍ መሰረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት አዋጅ የሳይበር ደህንነትን በማረጋገጥ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም መከበር ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ገለጹ። ዋና ዳይሬክተሯ ትዕግስት ሃሚድ አዋጁን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ አዋጁ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁን ጠቅሰዋል። ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ የኢትዮጵያን የዲጂታል ሽግግር ጉዞ በጠንካራ የሳይበር ደህንነት መሰረት ላይ ለመገንባት የሚያስችል መሆኑንም አንስተዋል። የዲጂታል መታወቂያ መርሃ ግብር፣ የሞባይል ክፍያና የኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓት እና መሰል ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ከፍተኛ መጠን ያለው ዳታ እንደሚያመነጩ አመልክተው፤የእነዚህን መረጃዎች እና ሲስተሞች ደህንነት ማረጋገጥ ወሳኝ ነው ብለዋል። በመሆኑም የአዋጁ ወደ ስራ መግባት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የዜጎች እና የሀገርን መረጃ ከጥቃት በመጠበቅ የመረጃ ሉዐለዊነትን ለማረጋገጥ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አብራርተዋል። በቁልፍ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚቃጡ ጥቃቶች እየጨመረ መምጣት ለአዋጁ መውጣት ምክንያት መሆኑን ገልጸው፤አዲሱ አዋጅ የሳይበር ስጋትን መሰረት ያደረገ ቁጥጥር እና የተማከለ የክስተት ምላሽ ስርአትን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። በአዋጁ መሰረት አስተዳደሩ ቁልፍ መሰረተ ልማት ተቋማት ማሟላት በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ማገዝ ፣ ለቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ የሚረዱ መመሪያዎችና ስታንዳርዶችን ማዘጋጀት በህግ ማዕቀፉ ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል እንደሚገኝበት አክለዋል። በቁልፍ መሰረተ ልማት ጥበቃ ዙሪያ ብቁ ባለሙያና በስነ ምግባር የታነጸ የሰው ሃይል የማደረጀት ስራዎች ይሰራሉም ብለዋል። በአዋጁ ዙሪያ ለህብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባራት እንደሚከናወኑም ገልጸዋል። ቁልፍ መሰረተ ልማት ባለቤት የሆኑ ተቋማት ደግሞ የሰለጠነ ባለሙያ ማሰማራት፣ማብቃት እና ተገቢውን ደህንነት ማጣሪያ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አዋጁ እንደሚደነግግም ጠቁመዋል። ከሳይበር ጥቃት ራሳቸውን መጠበቅ የሚችሉበት ቴክኖሎጂዎችን መታጠቅ ከተቋማቱ የሚጠበቅ ሌላው ሃላፊነት መሆኑን አብራርተዋል።
የሲቪል ምዝገባ የዲጂታል ስርዓት ዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ እያስቻለ ነው
Aug 6, 2026 278
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የጀመረው ዲጂታል የአሰራር ስርዓት ዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ እያስቻለ መሆኑን የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አሰራሩን ለማዘመንና ለማቀላጠፍ አገልግሎቶቹን በኦንላይን በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ የኦንላይን አገልግሎቱ ገፅ ለ ገፅ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች በተሻለ ሁኔታ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው በሞባይል፣ በላፕቶፕና በሌሎች ዲጂታል መሳሪያዎች በአጭር ጊዜ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሤ ለኢዜአ እንደገለጹት ፤ ተቋሙ በአጠቃላይ ከሚሰጣቸው ሰባት ዋና ዋና አገልግሎቶች መካከል በአሁኑ ወቅት የመታወቂያ፣ የልደት እና ያላገባ ማረጋገጫ አገልግሎቶችን በኦንላይን እየሰጠ ይገኛል። እስከ አሁን ከ15 ሺህ በላይ ተገልጋዮች በኦንላይን ሥርዓቱ አገልግሎት ማግኘታቸውን የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሩ፤ አዲሱ አሰራር የተገልጋዮችን ጊዜና ወጪ ከመቆጠቡም በላይ እንግልትን እያስቀረ መሆኑን አስረድተዋል። በተጨማሪም አሰራሩ ለባለሙያዎች ምቹ የሥራ ሁኔታ በመፍጠር የሥራ ቅልጥፍናንና ውጤታማነትን ማሳደጉን ገልጸዋል። ኤጀንሲው መረጃዎችን በዲጂታል ሥርዓት በማደራጀት ዘመናዊ የኦንላይን አገልግሎቶችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በቀጣይም የጋብቻ፣ የፍቺ፣ የሞትና የጉዲፈቻ አገልግሎቶችን ጨምሮ ሌሎችንም አገልግሎቶች ወደ ኦንላይን ሥርዓት በማስገባት ተደራሽነታቸውን ለማሳደግ እየሠራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ከዚህም በተጨማሪ ከጤና ተቋማትና ከፍርድ ቤቶች ጋር በመቀናጀት እንደ ልደትና ሞት ያሉ ኩነቶች በተከሰቱበት ቦታ ላይ በቀጥታ እንዲመዘገቡ የሚያስችል አሰራር እየተጠናከረ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። በኤጀንሲው እየተከናወነ ያለው ይህ የዲጂታል ሽግግር የኢትዮጵያን የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ እና የከተማዋን የስማርት ከተማ ግንባታ ግብ እውን ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረውም አብራርተዋል፡፡ አገልግሎቱን የበለጠ ተደራሽ ለማድረግ በመገናኛ ብዙኃንና በተለያዩ አማራጮች ህብረተሰቡ ስለ ኦንላይን አገልግሎቱ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታ ሀገሪቱ ግቧን በፍጥነት ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት ያሳያል
Aug 5, 2026 472
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሀገሪቱ ግቧን በፍጥነት ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን የቤኒን የዲጂታል ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን ገለጹ፡፡ በቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የተመራ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ የአምስት ቀን የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ መግባቱ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ሚኒስትሩና የልዑካን ቡድናቸው በኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትና በፋይዳ ቨርስ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ በቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ፈጣን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግር እየተደረገ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን በአጭር ጊዜ አስገራሚ የዲጂታል መሰረተ ልማት በመገንባትና ፈጣን የመንግሥት አገልግሎት ስርዓት ላስመዘገቡት ዕምርታ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያና ቤኒን መካከል ያለው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክፍተት በጋራ መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ልምድ መለዋወጥ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሀገሪቱ ግቧን በፍጥነት ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት በግልጽ እንደሚያሳይ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በዲጂታል መሰረተ ልማት እያደገች መሆኑን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ከዚህ መማር አጀንዳችንን ለማቀላጠፍ ያግዘናል ብለዋል፡፡ ቤኒን በሳይበር ደህንነት ያላትን ጠንካራ አቅም ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለማሳደግ በአቅም ግንባታና በዕውቀት ልውውጥ በጋራ መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡ የፋይዳ ቨርስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮዳሔ አርዓያሥላሴ በበኩላቸው፤ የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ለኢትዮጵያ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል፡፡ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ለዲጂታል ዲፕሎማሲ አቅም ግንባታ የጎላ አበርክቶ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ብዙ የተለመደው ከአውሮፓ ወይም ከኤዥያ የሚመጣን ስርዓት ማስተዳደር ነው ያሉት አቶ ዮዳሔ፤ ቴክኖሎጂን በራስ አቅም መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ሁሉም መገንዘቡን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የራሷን ቴክኖሎጂዎች በማፍለቅ ለሌሎች ትምህርት መስጠቷ አፍሪካውያን በራሳቸው እንዲተማመኑና ዕምነት እንዲኖራቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ስያሜውንና ተልዕኮውን በመቀየር ራሱን ችሎ የመንግሥት የልማት ድርጅት ሆኖ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥር መካተቱን አንስተዋል፡፡ ይሄውም አገልግሎቱን ከኢትዮጵያ ውጪ በማስፋት በአፍሪካ ሀገራት ጭምር የማማከርና ስርዓት የመገንባት ዕድሎችን የምናገኝበት ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ የኢፌዴሪ የመሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮናስ አለማየሁ፤ መሶብ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን አሻሽሏል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ 108 የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በመክፈት ከ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ማገልገል ተችሏል ብለዋል፡፡ ከ220 በላይ አገልግሎቶችን በላቀ ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊ አሰራር በመስጠት የተገልጋዮችን እርካታ 98 በመቶ ማድረስ እንደተቻለም ገልጸዋል፡፡ መሶብ የኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ የመሻገር ህልም መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ ሀገራት ልምድ የሚወስዱበትና የዲፕሎማሲ ተግባቦት የሚፈጠርበት ነው ብለዋል፡፡ የቤኒን ብቻ ሳይሆን የሌሎች ዓለም ሀገራት ጭምር አይተው የሚደነቁበት መሆኑን በማንሳት ጉብኝቱ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ብዙ ርቀት መጓዟን እንደሚያሳይ ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን ኢንጂነሮችና በኢትዮጵያ ሀብት የለማ መሆኑ ኢትዮጵያውያን እውቀትና አቅማችንን አስተባብረን መስራት እንደምንችል አሳይቷል ብለዋል፡፡
ስፖርት
የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች የወጣቶችን ስብእና የመገንባት ሚና አላቸው
Aug 9, 2026 49
ደብረ ብርሃን፤ ነሐሴ 3/2018(ኢዜአ)፡-የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች የወጣቶችን ስብእና ለመገንባት ሚና እንዳላቸው የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ውድድርን ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ አስጀምሯል። የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ በዚህ ወቅት እንደገለጹት ከተማዋን የቱሪዝም፣ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማእከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። በተለይም የስፖርት ዘርፉን በማሳደግ ጤናማና አምራች ዜጋ ለማፍራትና በሀገር እና ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ወጣቶችን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማ አስተዳደሩም ባለሀብቱንና ማህበረሰቡን በማስተባበር በየጊዜው የሚካሄዱ የታዳጊዎች ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድርን በልዩ ትኩረት እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል። በክረምት ወቅት ወጣቶች ገዜያቸውን የሚያሳልፉበትን ስፖርታዊ ውድድር ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ የተጀመረው ውድድርም የዚህ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ተክለዮሐንስ ኃይለጊዮርጊስ በበኩላቸው የክረምት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች ታዳጊዎች የእረፍት ጊዜያቸውን በአልባሌ ስፍራ እንዳያሳልፉ ለማድረግ ታስቦ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። ዛሬ በተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች እግር ኳስ ውድድር በ60 ቡድኖች የታቀፉ 1ሺህ 500 ስፖርተኞችን በማሳተፍ የሚካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። የውድድሩ ዓላማ ወጣቶች በስፖርታዊ ስነ ምግባር ከመታነጽ ባለፈ ተሰጧቸውን አውጥተው በማሳየት በቀጣይ ለትልልቅ ክለቦች የሚመረጡበትን እድል የሚከፍት ነው ብለዋል። በተለይም ስፖርት ለሰላምና ለአንድነት ያለውን አበርክቶ በመጠቀም ወጣቶች አንድነታቸውን በማጠናከር ለአካባቢያቸው ሰላምና ልማት በጋራ እንዲሰለፉ ለማድረግ እንደሚካሄድ አስረድተዋል። "የኮኮብ እግር ኳስ ቡድን" አሰልጣኝ ሐብታሙ መለሰ፣ የክረምት ውድድር መዘጋጀቱ ታዳጊዎች በስልጠና ያገኙትን የቴክኒክ እውቀት በተግባር የሚያሳዩበት ዕድል ይፈጥርላቸዋል ብለዋል። "የአንድነት እግር ኳስ ቡድን" አሰልጣኝ ታምራት ደስታ በበኩላቸው ውድድሩ የባህል ልውውጥ በማድረግ አንድነትንና መተሳሰብን ለማጎልበት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል በደብረ ብርሃን ከተማ ዛሬ የተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ውድድር ለአንድ ወር የሚካሄድ መሆኑ ተመላክቷል።
የዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ዛሬ ፍጻሜውን ያገኛል
Aug 9, 2026 90
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦ 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጠናቀቃል። ከሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአሜሪካ ኦሬጎን እየተካሄደ ባለው ሻምፒዮና ከ147 ሀገራት የተወጣጡ ከ1800 በላይ አትሌቶች ተሳታፊ ሆነዋል። ኢትዮጵያም በሻምፒዮናው ላይ ተሳትፎ እያደረገች ሲሆን እስከ አሁን ሁለት የወርቅ፣ ሶስት የብር እና አንድ የነሐስ በድምሩ ስድስት ሜዳሊያዎችን በማግኘት ሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። አሜሪካ በስምንት ወርቅ፣ ስድስት የብር እና አራት የነሐስ በድምሩ 18 ሜዳሊያዎችን በማግኘት አንደኛ ደረጃን ይዛለች። ጣልያን በሶስት ወርቅ እና ሁለት ነሐስ በድምሩ አምስት ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። እስከ አሁን 35 ሀገራት የሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ ገብተዋል። ሻምፒዮናው ዛሬ ማምሻውን በሄይዋርድ ፊልድ ስታዲየም ይጠናቀቃል።
ኢትዮጵያ በ20 ዓመት በታች የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ሁለተኛ የወርቅ ሜዳልያ አሳካች
Aug 9, 2026 120
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 3/2018 (ኢዜአ)፦በአሜሪካ ኦሬጎን እየተካሄደ ባለው 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ኢትዮጵያ ሁለተኛ የወርቅ ሜዳልያ አሳክታለች። ዛሬ ማለዳ በተደረገው ከ20 ዓመት በታች የዓለም አትሌቲክስ የ3000 ሜትር ውድድር አትሌት ዮርዳኖስ ፅጋብ የወርቅ ሜዳሊያ አሸንፋለች። አትሌቷ 8:43.65 የሆነ የግል ምርጥ ሰዓቷን በማስመዝገብ ነው ለሀገሯ የወርቅ ሜዳልያ ያስገኘቸው። ሌላኛዋ አትሌት ሽቶ ጉሚ 8:45.06 በሆነ ሰዓት ውድድሯን ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቅ የብር ሜዳልያ አሳክታለች። አትሌቷ በተመሳሳይ በ5000 ሜትር የብር ሜዳልያ ማግኘቷ ይታወሳል። በአሜሪካ ኦሪገን እየተከናወነ የሚገኘው ከ20 ዓመት በታች የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ዛሬ ይጠናቀቃል። ኢትዮጵያ በውድድሩ 2 ወርቅ ፣ ሦስት ብር እና 1 ነሐስ ሜዳልያ በመሰብሰብ በሜዳልያ ሰንጠረዡ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ብሩኖ ጉማሬሽ አርሰናልን በይፋ ተቀላቀለ
Aug 8, 2026 159
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የኒውካስል ዩናይትድ አምበል የነበረውን የ28 ዓመቱን የብራዚል ብሔራዊ ቡድን አማካይ ብሩኖ ጉማሬሽን ዝውውር ማጠናቀቁን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የወቅቱ የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው አርሰናል ለተጫዋቹ ዝውውር የ75 ሚሊዮን ፓውንድ ክፍያ የፈጸመ ሲሆን፣ ጉማሬሽም ተጨማሪ የአንድ ዓመት ማራዘሚያ አማራጭ ያለው የአራት ዓመት ውል ተፈራርሟል። በሚኬል አርቴታ ስብስብ ውስጥ 39 ቁጥር ማሊያን ለብሶ ይጫወታል። ብሩኖ ጉማሬሽ ዝውውሩን አስመልክቶ በሰጠው አስተያየት አርሰናልን መቀላቀል የፈለገው አዲስ ፈተናን ለመጋፈጥ እና ትላልቅ ዋንጫዎችን ለማንሳት መሆኑን ገልጿል። የ28 ዓመቱ ተጫዋች እ.አ.አ ጁላይ 2026 ላይ አርሰናልን ለመቀላቀል በግሉ ተስማምቶ እንደነበር የሚታወስ ነው። አሁን ላይ ጉማሬሽ አርሰናልን መቀላቀሉ የተንዛዛውን የዝውውር ጉዳይ እንዲቋጭ አድርጎታል። ጉማሬሽ እ.አ.አ በ2022 ከሊዮን ወደ ኒውካስትል ዩናይትድ በመዘዋወር ሲጫወት ቆይቷል። ተጫዋቹ መድፈኞቹን መቀላቀሉ የቡድኑን የአማካይ ክፍል ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ይጠበቃል። ብሩኖ ጉማሬሽ ከክሪስቶስ ዞሊስ እና ኢላን ሜስሊዬር በመቀጠል አርሰናል በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት የተቀላቀለ ሶስተኛ ተጫዋች ሆኗል።
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ አስችለዋል
Aug 8, 2026 105
ጂግጂጋ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ አስችለዋል። 3ኛው ዙር የአካባቢ ብክለት መከላከል ክልል አቀፍ ንቅናቄ ''ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ'' በሚል መሪ ሐሳብ በጂግጂጋ ተካሄዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን እንደገለጹት፣ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ አስችለዋል። ጽዱ ኢትዮጵያን እውን ለማድረግም የፕላስቲክ ነክ ተረፈ ምርቶችን፣ የደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ብክለትን በመከላከል በውሃ እና አፈር ላይ እየተፈጠረ ያለውን ተጽዕኖ ለመቀነስ የወጡ ህጎችና መመሪያዎችን ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም የቆሻሻ ማስወገጃ ዘላቂ ሥርዓቶችን በመገንባት ከተሞች ምቹና ጽዱ እንዲሆኑ በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የአከባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ በበኩላቸው፣ መርሃ ግብሩ ባለፉት ሁለት ዙሮች የተገኙ ውጤቶችን በማጠናከርና፣ በማስፋት፣ ጤናማና ንጹህ አካባቢን የመፍጠር ተግባሩን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን አመልከተዋል። ''እንዲሁም አካባቢያችንን ለመጠበቅ እና ለመጪው ትውልድ ፅዱ ኢትዮጵያን ለማውረስ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ ለማረጋገጥም ጭምር ነው'' ብለዋል። 3ኛው ዙር የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ በቀጣዮቹ ሶስት ወራት የሚተገበርና በዋናነት የፕላስቲክ ብክለትን በመከላከል፣ አደገኛ ኬሚካሎችንና ቆሻሻዎች አያያዝን፣ እንዲሁም የድምፅ ብክለትን የመከላከል ተግባራት እንደሚከናወንም አክለዋል። እንደ ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ ገለጻ፤ ፅዱ ኢትዮጵያ በመንግስት ብቻ የሚከወን ባለመሆኑ በየቤታችን፣ በየትምህርት ቤቱ፣ በየመሥሪያ ቤቱና በፋብሪካዎች የምንፈጽማቸው በጎ ተግባራት ተደምረው ትልቅ ሀገራዊ ለውጥ ያመጣሉ። በዚህም ሁሉም የመንግስት ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የሴቶችና የወጣቶች ማህበራት እንዲሁም እያንዳንዱ ዜጋ የዚህ ሀገራዊ ንቅናቄ ባለቤት በመሆን በንቃት እንዲሳተፍም ጥሪ አቅርበዋል። የሶማሌ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አስተዳድር ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ሙህየዲን አብዲ በበኩላቸው በክልሉ ባለፉት ዓመታት በጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄዎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ጽዱ አካባቢ ለመፍጠር እየተከናወኑ የሚገኙ በርካታ ተግባራትም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የቢሮ ኃላፊው አረጋግጠዋል። በመርሃ ግብሩም በክልሉ ፕላስቲክን በመከላከል፣ መመሪያዎችን በመተግበርና ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ውጤታማ የሆኑ ከተሞች የእውቅና መስጠት ሥነ-ሥርዓት ተካሄዷል።
አረንጓዴ አሻራ ለትውልድ የሚተላለፍ ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃ ባህል ነው
Aug 8, 2026 117
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያውያን ለትውልድ የሚያስተላልፉት ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃ ባህል ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎት ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ሃላፊዎችና ሠራተኞች፣ ’’ተስፋን እንትከል’’ በሚል መሪ ቃል በእንጦጦ ሸገር ፓርክ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናውነዋል። የባንኩ የኮርፖሬት አገልግሎት ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ አረንጓዴ አሻራ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮችን መቋቋም ያስችላል። በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ስራዎች የታዩ ተጨባጭ ለውጦች መኖራቸውን አንስተው፣ በተለይም ለአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ስነ ምህዳሯ የተጠበቀና አረንጓዴ አገርን ለቀጣይ ትውልድ ለማስረከብ ችግኝ መትከልና መንከባከብ ወሳኝ ሀገራዊ ሀላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ ባንኩ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ250 ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን ገልጸው፤አረንጓዴ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ጠንካራ የኢትዮጵያዊያን የአካባቢ ጥበቃ ባህል መሆኑን ተናግረዋል። የባንኩ አመራሮች እና ሰራተኞችም በዚህ ታላቅ ሀገራዊ መርሀግብር የሚያደርጉትን ተሳትፎ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የህዝብን አቅም በማስተባበር የተከናወነ ታሪካዊ ስኬት ነው
Aug 7, 2026 189
ጅማ ፤ ነሃሴ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በመደመር መንግስት እሳቤ የህዝብ አቅምን በማስተባበር የተከናወነ ታሪካዊ ስኬት መሆኑን የጅማ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። የመደመር መንግሥት የተበታተነን አቅም በማቀናጀትና የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ በማጎልበት፣ በአንድ ቀን ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን መትከልን የመሰሉ በተግባር የተገለፁና የሚገለፁ እውነታዎችን የያዘ እሳቤ ነው። ይህም የኢትዮጵያውያን በጋራ መቆም፣ የውስጥ አቅምን አሟጦ መጠቀም እና የትብብር ባህልን ማሳደግ አዎንታዊ ለውጥ ለማምጣት እንደሚያስችል በተግባር ያረጋገጠና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጉዞ የሚያፋጥን ነው። ምሁራኑ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት እንደገለፁት፤ የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በመደመር መንግሥት እሳቤ የሕዝብ አቅምን በማስተባበር የተከናወነ ታሪካዊ ስኬት ነው። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ጥናት ትምህርት ክፍል መምህር ጌታቸው ጥላሁን (ዶ/ር) ፤ የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በመደመር መንግሥት እሳቤ የሕዝብ አቅምን በማስተባበር የተከናወነ ታሪካዊ ስኬት ነው ብለዋል። ይህንንም ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ለሀገራዊ ጥሪው ስኬት የድርሻውን በመወጣት ማሳየቱን ተናግረው ከመንግሥት ጎን በመቆምም ለኢኮኖሚው ዕድገት ያለውን ቁርጠኝነት መግለፁን ጠቁመዋል። ሕዝቡ በአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ያሳየውን የተቀናጀ መረዳዳትና ከፍተኛ ተሳትፎ፣ በሀገር ግንባታ፣ በኢኮኖሚ ዕድገት እንዲሁም በሕብረተሰብ አቀፍ በጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ ማስቀጠል የሚገባው መሆኑን አስረድተዋል። ባለፉት ዓመታት እየጎለበቱ የመጡትን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና የማዕድ የማጋራት እንቅስቃሴዎችን በምሳሌነት የጠቀሱት ምሁሩ፤ በጥቂቱ ታስቦ የተጀመረው ሥራ ትልቅ ደረጃ መድረስ እንደሚችል ማሳያ ነው ብለዋል። በተለይም በሁሉም ዘርፎች የተጀመሩ ዘላቂ የልማት ስራዎችን ከዳር ለማድረስ የዜጎች ሕብረትና አንድነት ወሳኝ መሆኑን የጠቆሙት ምሁሩ፤ ይህ የሕዝቡ ቀናነትና ለልማት የመቆም ባህል በሁሉም መስክ ሊስፋፋ እንደሚገባም አመልክተዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ሥነ-ምግብ መምህርና ተመራማሪ ዋሲሁን ሀሰን (ዶ/ር)፤ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ትልቅ ሀገራዊ ድል በመሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን በጋራ በመቆም የተቀዳጁትን የዓድዋን ድል የሚያስታውስ ነው ብለዋል። ሕዝባዊ ትብብርና መግባባት በሚገባ ከተፈጠረ በተሰማሩበት የሥራ ዘርፍ የሚፈለገውን ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ገልፀው ይህንንም ለሀገር ዕድገትና ብልፅግና ማዋል እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል አቅም እየተገነባ ነው
Aug 6, 2026 240
ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና ሀገራዊ ግቦችን ለማሳካት የሚያስችል አቅም እየተገነባ መሆኑን የውሀና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የሚኒስቴሩ እና የተጠሪ ተቋማቱ አመራሮች የአረንጓዴ አሻራና የበጎ አድራጎት መርሃ ግብርን በሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን በሸበዲኖ ወረዳ አካሄደዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና ሀገራዊ ግቦችን ለማሳካት የሚያስችል አቅም እየተገነባ ነው። በየዓመቱ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እየተተከለ ያለው ችግኝ የአካባቢ መራቆትና የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ የውሃ ምንጮችን በማጎልበት የውሃ ሀብት መጠንን ያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬውም መርሃ ግብር የዚሁ አካል እንደሆነ ጠቁመዋል። ከችግኝ ተከላው ጎን ለጎንም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሚኒስቴሩ አጋዥ የሌላቸው ወገኖችን በመደገፍ አጋርነቱን እያሳየ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዛሬው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሚኒስቴሩ በሸበዲኖ ወረዳ ዲላ አፈራራ ቀበሌ የሰባት አቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት አፍርሶ ለመገንባት መረከቡንና ቤቶቹ ደረጃቸውን ጠብቀው ተገንብተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ርክክብ እንደሚደረግም ገልጸዋል። የሲዳማ ክልል ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ከበደ ጋኖሌ በበኩላቸው፤ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባለፉት አምስት ዓመታት በመጠጥ ውሃና ኢነርጂ አቅርቦት ረገድ በክልሉ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል ብለዋል። በዚህም የክልሉ የመጠጥ ውሃ ሽፋን ወደ 75 በመቶ ማደጉንና በኢነርጂው ዘርፍ እየገነባቸው ካሉ አምስት ፕሮጀክቶች ሁለቱ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ገልጸዋል። በሚኒስቴሩ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ የውብዳር አሚኖ፤ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በአካባቢው የገጽና ከርሰ ምድር ውሃን በማጎልበት ውሃ ፍለጋ ረጅም ርቀት የሚጓዙ እናቶችን ድካም አስቀርቷል ብለዋል። የሰሜን ሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፃዲቁ ባጢሶ፤ ሚኒስቴሩ በመጠጥ ውሃ አቅርቦትና በኢነርጂው ዘርፍ እያከናወነ ያለው ተግባር በዞኑ በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቁመው፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎትና በችግኝ ተከላው እያበረከተ ላለው አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በሸበዲኖ ወረዳ የዲላ አፈራራ ቀበሌ ነዋሪው አቶ አበራ ካሼራ ቤታቸው በመፍረሱ በክረምት ዝናብና ብርድ ሲፈተኑ መቆየታቸውን ገልጸው አሁን ቤታቸውን ሊታደስላቸው በመሆኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ ለ500 ተማሪዎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው ሲሆን፣ የሚኒስቴሩና ተጠሪ ተቋማቱ ሠራተኞች የፍራፍሬና ሌሎች ሀገር በቀል ችግኞችን ተክለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 406
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 437
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች። ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 734
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 1212
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር!
Aug 9, 2026 151
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር! በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን ) የገጠሩ ማህበረሰብ የጨለማ ኑሮ የተፈረደበት ይመስል ኑሮውን ማሻሻል ሳይችል እልፍ ዓመታት ተቆጥረዋል፤ ለዘመናት መብራትና ውኃ ለማግኘትና ከቴክኖሎጂ ጋር ተቀራርቦ ለመኖር ወደ ከተማ መሰደድ ብቸኛው አማራጭም ነበር። የከተሜው ዋልታ የሀገር ኢኮኖሚ መሠረት የሚወሰንበት የአራሹ ገበሬ የኑሮ ደረጃ ባህላዊውን የአኗኗር ዘዬ ባለመልቀቁ ደስተኛ ጊዜ የሚያሳልፍበት ሂደት አድካሚ እንደሚሆን ግልጽ ነው። የገጠሬው የተበታተነ የአኗኗር ሥርዓትም ለገጠሬው አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፤ የእዚህን የህብረተሰብ ክፍል ምርቱን እንጂ ኑሮውን የጠየቀ አልነበረም ቢባል ግነት አይሆንም። ቀደም ሲል በነበሩ መንግስታት ከተማን እንጂ ገጠርን ማዘመን የሚያስብ ስለመኖሩ ያጠራጥራል፤ ይህም በሀገሪቱ ለኢፍትሐዊ ዕድገት የራሱን ተጽዕኖ ሲያሳደር ቆይቷል። የመደመር መንግሥት ግን ይህን ቀይሮታል። ሀገር የመምራት ኃላፊነት ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ በከተማና በገጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ በዜጎች የኑሮ ሥርዓት ላይ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርጎ እየሰራ ነው ከተሜነት ብቻውን አድጎ የገጠሩ ማኅበረሰብ በቀድሞ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሆነ የተሟላ ዕድገት ማምጣት አይቻልም የሚል ጽኑ እምነት አለው። በእዚህም ከተማና ገጠርን ለማቀራረብ በገጠር ትራንስፎርሜሽንን የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ቀርጾ መተግበር ከጀመረ ከራርሟል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን አንዱ አካል የሆነው የገጠር ሞዴል መንደር በአርሶ አደሮች ዘንድ የሚጨበጥ ተስፋን ይዘው ከመጡ ኢኒሼቲቮች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው። ከተስፋ ተሻግረው በዚህ ሞዴል መንደር የነዋሪነት ዕድልን ያገኙት ደግሞ ብርሃን አይተዋል፤ የትናት አኗኗራቸውን የቀየረ አዲስ ዛሬን በእጃቸው አድርገዋል፤ ነገን አልቀው መመልከት የግብርና ተግባራቸው አንዱ አካል ሆኗል። በአዲሱ መንደራቸው ዛሬ የሚያፈስ ቤት የለም፣ የእንስሳት ቆሻሻ ሽታ በአፍንጫቸው አይገባም፣ በሚቆረቁር እንጨት ወይም መደብ ላይ አይቀመጡም፤ የከተሜው መዘነጫ ሶፋ በሳሎናቸው ተከስቷል። ጓሮዎቻቸው ሁሉ ሙሉ እንደሆኑ አፍ አውጥተው የሚያወሩ ናቸው። በዚህ ቆስጣ፤ በዛ በኩል ጎመንና ቀይስር፤ ዘውር ሲሉ ደግሞ ከአስር የሚልቁ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፤ በአንድ ክፍል ደግሞ እናት ላም ከጥጃዋ ጋራ፣ የእንቁላል ዶሮ ከሥጋ ዶሮ ጋር ሁሉንም በአንድ ጊቢ ውስጥ ያገኛሉ። ምን ይሄ ብቻ አቮካዶ እና ፓፓያ፣ ሙዝና እንሰት፣ በርበሬና ሽንኩርት ሳይቀር ለተትረፈረፈ የአርሶ አደር ማዕድና ገበያ ራሳቸውን አዘጋጅተዋል። አርሶ አደር ኃይሉ ሞትንሞስ በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የጌሊት ሞዴል መንደር ነዋሪ ናቸው። እርሳቸው "መንግስት ጨለማችንን ገፎ ብርሃን አሳየን" ሲሉ በጠንካራ ቃላት የገጠር ሞዴል መንደር ፕሮጀክት ያመጣላቸውን በጎ ነገር ይገልጻሉ። እውነት ነው ያላዩትን ብዙ ነገር አሳይቷቸዋል። ያም ብርሃን ቤት ውስጥ የሚበራ ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው፣ በነገ ተስፋቸውና በኢኮኖሚያቸው ላይ የፈነጠቀ ብርሃን ነው። ዛሬ ያሉበትን ህይወትም "ለእኔ አዲስ ነገር ነው። አይቼው አላውቅም፤ መቼም በራሴ ሀሳብ አላደርገውም ነበር።" ሲሉ ይገልጻሉ። መንግስት አበራልኝ ያልኩት በእጄ ያለኝን ያላየሁትን ዕድል ስላሳየኝ ነው በማለትም ሀሳባቸውን ይቀጥላሉ። እኛ ሀብት አለን፤ ሀብታችንን የምንጠቀምበት መንገድ ግን ትክክል አይደለም። ይልቁንም የምናባክነው ይበዛል በማለትም የቀደመ ሕይወታቸውን እያሰቡ ይቆጫሉ። አሁን ግን ብዙ ተገነዘብኩ የሚያስብል የመደመር መንግስት በመኖሩ አዲስ ሕይወት በአዲስ ተስፋ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። እርግጥ ነው የገጠር ሞዴል መንደር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ነው። ለአብነትም የማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ መሠረተ ልማት ዝርጋታን ማንሳት ይቻላል። የተሠሩ ሞዴል መንደሮች በመጀመሪያ የመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ የመሆን ዕድል ገጥሟቸዋል። በመቀጠል ንጽሕናው ያልተረጋገጠ የመጠጥ ውኃ ወንዝ ወርዶ ከመቅዳት ተቆጥበው በመንደራቸው የተገነባውን የከረሰ ምንድር ውሃ ከቧንቧ ቀድተው መጠጣት አስችሏቸዋል። በእሳት እና ኩራዝ ጭስ ሲሰቃዩ የነበሩ ዓይኖቻቸው ዛሬ ከሶላር ቴክኖሎጂ የመነጨ ብርሃን ማየት ጀምረዋል። ብርሃን ብቻ አይደለም ለወትሮ ለገበያ ወደ ከተማ ብቻ ሲወጡ ይመለከቱ የነበረውን ቴሌቪዥን ዛሬ በቤታቸው አስገብተው የመረጃና የመዝናኛ ዓለምን ተቀላቅለዋል። አርሶ አደሮቹ ቴሌቭዥንን ከመዝናኛነት ይበልጥ ለመረጃ እንደሚጠቀሙት ያነሳሉ። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በዜና ተከታትሎ መረዳት፣ የገበያ ሁኔታን ማወቅ፣ የግብርና ሥራ ተሞክሮን መቅሰምና የአየር ንብረት ሁኔታን ጨምሮ ለሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙት ከቴሎቪዥን መስኮት እንደሆነ ይናገራሉ። በጓሯቸው የተትረፈረፈ የሌማት ትሩፋት ምርት መሰብሰብ የሚያስችላቸው ምቹ ሁኔታ ደግሞ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው። በተለይ መንግስት በጓሯቸው ጥምር እርሻ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ የነገ ኢኮኖሚያቸውን በአስተማማኝ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ ነው። ከተማን መናፈቅን ያስቀረው የገጠር ሞዴል መንደር ያኔ ከጅምሩ አመኔታን አላገኘም። የቦታና የአካባቢ ቁሳቁስ ለማቅረብ ዝግጁ እስካለመሆን የደረሱ አርሶ አደሮችም ነበሩ። በወቅቱ ጉዳዩን እንደፌዝ አዩት። ዛሬ ግን ውጤቱን በአግራሞት በዐይናቸው ተመለከቱ። የተናገረውን የሚከውን፤ የጀመረውን የሚጨርስ የመደመር መንግሥትን ተጨባጭ ስራዎች በማረጋገጥ እንደ ትንግርት ቆጠሩ። ዛሬ በየአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች በቁጭት ተሞልተው መንደራቸውን ወደዚህ የሞዴል መንደር እሳቤ ለመቀየር ተነሳስተዋል። የጌሊት ቀበሌ አርሶ አደሮቹ መኮንን አርዶ እና ነጻነት ተስፋሁን ለዚህ ተጠቃሾች ናቸው። ያዩትን ተሞክሮ በራስ አቅም በመንደራቸው ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ከተማ ሄደን የምናወጣውን ወጪና የምናባክነውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት እዚሁ መዝናናት የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ብለዋል። "ይህ ዕድል ለእኛ ለአርሶ አደሮች በታሪክ የሚነገር ትልቅ አጋጣሚ ነውም" ይላሉ። በጤዛ እየራስን እንጓዝበት የነበረው መንገዳችን ዛሬ ሰፍቷል። ተሽከርካሪ በደጃችን ስለሚያልፍም ምቹ ዕድልን ይዞልን መጥቷል። ይህን ጅምር ተግባር ወደ ላቀ ውጤት ማሸጋገር የእኛ ድርሻ ነውና ጠንክረን እንሠራለንም ብለዋል። ይህን ዕድል ወደ ትልቅ አቅም ለመቀየር መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳ የሸሸቃ ሞዴል መንደር ተጠቃሚ አርሶ አደር አልዓዛር ዘርክናንስ ናቸው። የዶሮና የከበት እርባታን እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ማነብ ሥራን ከመደበኛው የእርሻ ሥራ ጋር አስተሳስረው በመሥራት ከቤተሰብ ፍጆታ ተርፎ ለገበያ የሚበቃ ምርት ለማምረት እየተዘጋጁ ነው። ይህም የገቢ አቅማቸውን ከማሳደግ ባለፈ ልጆቻቸው ወተትና የወተት ተዋጽኦ በቤታቸው እንዲያገኙ ያደርጋል። ማር፣ እንቁላል እና ሥጋ እንዳያምራቸው የሚያደርግ ትልቅ ኢኒሼቲቭም ነው። አንዱ ቢጎድል በሌላው እየሞሉ የሚኖሩበትን የሥራ መስክ አጠናክረው ለውጤት አብቅተው ለተሻለ ለውጥ እንደሚሠሩ አክለዋል። የአርሶ አደር እናቶች ዘምቢል ይዘው አትክልትና ፍራፍሬ ሸመታ ወደ ገበያ ማቅናት የለባቸውም። ይልቁንም ከጎሮቸው ወደ ገበያ ይዞ መውጣት የኑሮ ዘዬያቸው ወግ ነው። ወይዘሮ መሠረት ማሞ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የበቆ ሞዴል መንደር ነዋሪ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ያልለመዱትን አዲስ ሕይወት ከአዲስ ተስፋ ጋር መጀመራቸውን ከሚናገሩት መካከል ናቸው። ትናንት ኩሽናቸው፣ መኝታቸው እንዲሁም የከብትና የዶሮ ማደሪያ በአንድ ቤት ወስጥ የተወሰነ እንደነበር ያስታውሳሉ። ዛሬ ግን ሽንት ቤትና መታጠቢያ ቤት ሳይቀር ለየብቻ የራሱ የሆነ ቤት ተገንብቶ ጽዳቱ የተጠበቀ ኑሮ መኖር ጀምረዋል። ቤታቸው ሲገቡና ሲወጡ ለዓይን ማራኪ፤ ለመቀመጥ ምቹ፤ ለመተኛትም ንጹህና ወገብ የሚያሳርፍ ሆኖ አግኝተዋል። እናም በዚህ እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ። "መንግስት እንደ አባት ጎዶሏችንን ሞልቷል" ሲሉም ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት ይህ የአርሶ አደሮችን ሕይወት ብሩህ ያደረገው የገጠር ሞዴል መንደር ኢኒሼቲቭ በመላው ሀገሪቱ በመስፋፋት ላይ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 16 ሞዴል መንደሮች በ16 ወረዳዎች ተገንብተዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት ኢኒሺዬቲቩ የአርሶ አደር ኑሮ ዘዬን ከማሻሻል ባለፈ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ ጋር ለማቆራኘት ያስቻለ ነው። የተሻለ መኖሪያ ቤት ኖሮት በጓሮው የሚበላ ነገር ካጣ ሕይወቱ ትርጉም ያለው ለውጥ አያመጣም። ይህም በመሆኑ ቤቶቹን ከእያንዳንዱ የግብርና ልማት ዘርፎች ጋር በማጣመር እንዲገነቡ የተደረገው። ይህም የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል ሀገራዊ ስትራቴጂን የሚያጠናክርና ገበያን የማረጋጋት ዓላማን የያዘ ጭምር ነው። በገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ የተገኘው መልካም ውጤት በቀጣይ በሁሉም ወረዳዎች የሚስፋፋ ሲሆን በዞን እና ወረዳ መዋቅሮች ድጋፍና ክትትል በቀበሌ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አንስተዋል። ይህ ኢኒሼቲቭ የሀገራዊ ብልጽግና ጉዞ አንዱ አቅም ነው። የተደመረ የማኅበረሰብ ብልጽግና ሀገርን ከፍ ያለ የዕድገት ማማ ላይ ያስቀምጣታል። እነሆ የክልሉ አርሶ አደሮች የአካባቢያቸውን ጸጋ ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ የሚቀይሩበት መስክ በሞዴል መንደር ምክንያት እጃቸው ላይ ደርሷል። አርሶ አደሮቹ እንዳሉትም በብዙ መንገድ ጨለማ የከበበው የገጠሩ ማኅበረሰብ ሕይወት ዛሬ ብርሃን ማየት ጀምሯል። ይህ የብርሃን ፋና እየተቀጣጠለ ወደ ብዙኃኑ ሊደርስ የሁሉንም ፍላጎት አነሳስቷል። ሥሩ ከማለት ይልቅ ሠርቶ ማሳየትን የሚያስቀድመው የመደመር መንግስት የፈጠራቸው የገጠር ሞዴል መንደሮች ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን በዘላቂነት የሚያሳምሩ ናቸው። ሰላም እንሰንብት!
ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የአፍሪካ ኃያል ሀገር እየሆነች ነው-ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት
Aug 7, 2026 385
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 1/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሪነት የመጪው ዘመን የአፍሪካ ኃያል ሀገር ወደመሆን እየተሸጋገረች ነው ሲል ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት ዘግቧል። ፈርስት ፖስት ሚዲያ ኢትዮጵያን በተመለከተ በሠራው ትንታኔው የሰው ዘር መገኛ፣የጥንታዊ መንግስታት ምድር፣የንግድ መስመሮች እና ከፍ ያለ የአፍሪካ ታሪካዊ መሰረት ያላት ሀገር መሆኗን አውስቷል። ሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ከቀድሞ ገናና ታሪኳ እኩል ታላቅ የሆነ አዲስ ምዕራፍ ለመገንባት በትጋት ላይ መሆኗን አንስቷል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት በቀጣናው እና የአፍሪካ ኃያል ሀገር መሆን የሚያስችላትን እንዲሁም የአህጉሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚበይንና የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሠራች መሆኗንም እንዲሁ። ለረጅም ዓመታት ዓለም ኢትዮጵያን የሚያውቃት በጦርነት፣በድርቅ እና በፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንደነበር በማስታወስ፥ዛሬ ግን ሀገሪቱ ይህንን የተዛባ ትርክት በኢነርጂ መሠረተ ልማት፣ በአቪየሽን፣ በማዕድን እና በዲጂታል ኢኮኖሚ አስደማሚ ለውጦች ለመቀየር እየሠራች ነው ብሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ተሻግራ እንዴት በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት ካላቸው ኢኮኖሚዎች ቀዳሚዋ ሆና ልትቀጥል ቻለች? የሚለውን ጥያቄ በማንሳትም በዝርዝር መልሶቹን ያብራራል። የዚህ ዋና ጥያቄ ዝርዝር ምላሽ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት እየተተገበሩ የሚገኙ የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ ነው ያለው ሲል አንስቷል። • የመጀመሪያው የኢነርጂ አብዮት እና ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ነው። በዚህ የኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ጎልቶ የሚነሳው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሲሆን፣ ከ5 ሺህ ሜጋዋት በላይ የማመንጨት አቅም ያለው የአፍሪካ ትልቁ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት መሆኑን ፈርስት ፖስት በዘገባው ጠቅሷል። ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መሻቶች መሰረት፣የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የውጭ ምንዛሬ እና የቀጣናዊ ተጽዕኖ መፍጠሪያ አቅም መሆኑንም አብራርቷል። የሕዳሴ ግድብ ልዩ የሚያደርገው የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ከዓለም ባንክ ወይም ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አንድ ሳንቲም ሳይበደር በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደም፣ ላብና ገንዘብ የተገነባ አፍሪካውያን በራሳቸው ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየነው ብሏል። ለኢትዮጵያውያን ግድቡ ከኮንክሪት እና ከተርባይን በላይ ትርጉም አለው ያለው ይህ የፈርስት ፖስት ዘገባ፥ እጅግ የላቀ እራስን የመቻል እና የኢኮኖሚ ነፃነት ማሳያ ሐውልት መሆኑንም ተንትኗል። ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን ለኬንያ፣ ለጂቡቲ እና ለሱዳን በመሸጥ ኤሌክትሪክን ወደ ከፍተኛ ገቢ ማመንጫነት እየቀየረች ከመሆኑም በላይ የመላው ምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የትስስር ማዕከል ሆናለች ነው ያለው። • የኢትዮጵያ የዕድገት ምሰሶ አቪዬሽን እና ቀጣናዊ ትስስር ኢነርጂ ብቻውን ኢኮኖሚያዊ አቅምን አይገነባም፤ ይልቁንም ኢነርጂ ኢንዱስትሪን ያነቃቃል፣ ትስስር ዓለም አቀፍ ንግድን ይመግባል ያለው ፈርስት ፖስት፥የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁን ለላቀ የዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ጉዞ መጀመሩን አንስቷል። በ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በየዓመቱ እስከ 110 ሚሊዮን ተጓዦችን እና ወደ 4 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ የዕቃ ጭነት ማስተናገድ አቅም አለው። ሙሉ በሙሉ ግንባታው ሲጠናቀቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከታላላቅ የአቪዬሽን ማዕከላት አንዱ ይሆናል ብሏል። ይህ ፕሮጀክት የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማሲ መናኸሪያ የሆነችውን አዲስ አበባንና አፍሪካን፣ከሌሎች የዓለም ክፍሎች የሚያስተሳስር ዋና የመተላለፊያ ማዕከል እንደሚሆንም ተገልጿል። ስለዚህ አዲሱ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንት እና ለቱሪዝም፣ ለዓለም የዲፕሎሲ ትብብር ጉልህ ሚና እንዲያበረክት ታስቦ እየተገነባ ነው ብሏል። • የማዕድን ኢንቨስትመንትና በምግብ ራስን መቻል በሌላ በኩል ከኢትዮጵያ መሬት በታች ላለው የማዕድን ሀብቷ ትኩረት በመስጠት የልማት አብዮት እያካሄደች ስለመሆኑም ተንትኗል። ሀገሪቱ የወርቅና ሌሎች ማዕድናት ማውጫ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት አዳዲስ የውጭ ምንዛሬ ምንጮችን እያፈራች የማዕድን ኢንዱስትሪዋን እያሳደገች ነው። ወርቅ በፍጥነት ከኢትዮጵያ ቀዳሚ የወጪ ንግድ ምርቶች አንዱ በመሆን ለረጅም ጊዜ በግብርና ላይ ብቻ ጥገኛ ሆኖ የቆየውን ኢኮኖሚ ወደ ብዝኃ ዘርፍ እያሸጋገረ ይገኛል። በሌላ በኩል በምግብ ራስን ከመቻል ውጭ የትኛውም ኢኮኖሚያዊ ለውጥ የተሟላ ሊሆን አይችልም ያለው የፈረስት ፖስት ዘገባ፥ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆኑን ጠቅሷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን እንድትችል በጀመረው የለውጥ ጉዞ አስደማሚ ውጤት እያመጣ ነው ብሏል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከጉባ ብስራቶች አንዱ የሆነውና በሶማሌ ክልል እየተገነባ የሚገኘው የማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት በየዓመቱ 3 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ ዩሪያ ማዳበሪያ ማምረት የሚችል ነው። ይህም ከውጭ የሚገባውን ማዳበሪያ ጥገኝነት በመቀነስ የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚያስችል አብራርቷል። "የምግብ ዋስትና የእኛ ስትራቴጂካዊ ጣልቃ ገብነት ነው።ያንን ግብ እውን ለማድረግ ግብአቶች ላይ መስራት አለብን።በግብአት ላይ መስራት ካልተቻለ የምግብ ዋስትናን እውን ለማድረግ መንገድ የለውም" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ በማካተት ዘገባው ሰፊ ሽፋን ሰጥቷል። ዲጂታላይዜሽን እና የኢንቨትመንትና የገበያ ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ለውጥ ወደ ዲጂታልም እየተሸጋገረ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እንደተናገሩት የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስልጠና ከዕቅዱ ቀድም ከመሳካቱም በላይ በርካታ ወጣቶች የዲጂታል እውቀት ባለቤት አድርጓል። በተመሳሳይ የዲጂታል ትስስር እየሰፋ ሲሆን የ4ጂ እና 5ጂ አገልግሎቶች በበርካታ ከተሞች ተደራሽ ሆኗል። ኢትዮጵያ ለበርካታ አስርት ዓመታት ተዘግተው የቆዩ እንደ ቴሌኮሙኒኬሽን፣ ባንክ እና የካፒታል ገበያዎች ያሉ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጓንም አድንቋል። የካፒታል ገበያን መጀመሯም የግል ካፒታል ልውውጥን በማጎልበት ለኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተንትኗል። እነዚህ ማሻሻያዎች በአጠቃላይ በመንግስት ቁጥጥር ስር ከነበረው የኢኮኖሚ ወደ ግል ዘርፍ ኢንቨስትመንት እያደገ የሚሄድ ኢኮኖሚ መሰረታዊ ለውጥን እየተገነባ መሆኑን ያሳያሉ ነው ያለው። ኢትዮጵያ ካላት የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ አኳያ እድልና ፈተናዎች ከፊቷ መሆናቸውን በማንሳት፥ አዲሱን የዓለም አቀፍ የትብብር ጥምረት ብሪክስ አባል መሆኗን አውስቷል። ከቻይና፣ ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት፣ ከምዕራባውያን አጋሮችና ከአፍሪካ ኢንቨስተሮች ኢንቨስትመንትን እየሳበች እንደምትገኝም እንዲሁ። ኢትዮጵያ ጎራ ሳትለይ ከሁሉም የዓለም ሀገራት ጋር ትብብሯን እያጠናከረች ነው ብሏል። ዓለም ኢትዮጵያን የምታስታውሰው በጦርነት ቢሆንም፥ኢትዮጵያ ዓለም በአዲሱ የለውጥና የስኬት ጉዞዋ እንዲያስታውሳት እየሠራች ነው። ለዚህም በመላው ሀገሪቱ በሁሉም ዘርፍ ግዙፍ የኢኮኖሚ ሽግግር እየተካሄደ ሲሆን፥ ይህ የኢትዮጵያ ጉዞ ለቀጣዮቹ ዓመታት የቀጣናውንና የአፍሪካን ኢኮኖሚያዊና አጠቃላይ ገጽታ በአዲስ መልኩ የሚቀርጽ ነው ሲል ፈርስት ፖስት ዘገባውን አብራርቷል።
ያቀደችውን በተግባር የምታሳካ ታላቅ ሀገር
Aug 3, 2026 703
የአንድ ሀገር ታላቅነት ከሚለካባቸው ጉዳዮች አንዱ የተያዙ ሀገራዊ እቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም ዋነኛው ነው። ኢትዮጵያም በዛሬው እለት በአንድ ጀምበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችው አዲስ ታሪካዊ ስኬት፣ ሀገሪቱ ያቀደችውን በተግባር ማሳየት የምትችልና ትልልቅ ህልሞችን የመተርጎም አቅም ያላት ታላቅ ሀገር መሆኗን ለመላው ዓለም በተግባር ያስመሰከረ ነው። ይህ በአንድ ጀምበር የተከናወነ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በርካታ ጥልቅ ትርጉሞችን የያዘ ነው፡ በአንድ ጀንበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ግዙፍ የሎጂስቲክስ፣ የዝግጅትና የህዝብ ንቅናቄ ስራን ይጠይቃል። ይህ ስኬት ሀገሪቱ ማንኛውንም ታላቅ አገራዊ እቅድ አቅዳ እስከ መጨረሻው የትግበራ ምዕራፍ ድረስ በብቃት የመምራትና የማስተባበር ተቋማዊና ህዝባዊ አቅም እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ዕድሜ፣ ጾታ፣ ወይም ልዩነት ሳይለያያቸው በአንድ ቀን ለተመሳሳይ አገራዊ ዓላማ መቆማቸው፣ ኢትዮጵያውያን ለጋራ እድገታቸውና ለሀገራቸው የወደፊት ተስፋ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎትና አንድነት አሳይቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት ዋና ስጋት በሆነበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ እርምጃ ለችግሩ መፍትሔ በመስጠት ረገድ የዓለም አቀፍ መሪነቷን ያስመሰከረችበት አጋጣሚም ጭምር ነው። ይህ ስኬት ሀገሪቱ የገጠሟትን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፈተናዎች ተሻግራ፣ አቅሟን አስተባብራ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ለዜጎቿም ሆነ ለውጭው ዓለም የሰጠችው ትልቅ የራስ መተማመንና የተስፋ መልእክት ነው። በአጠቃላይ፣ በአንድ ጀምበር የተከናወነው ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ አርቆ የማሰብና የማቀድ ችሎታዋን ብቻ ሳይሆን፣ ያቀደችውንም በአንድነትና በቁርጠኝነት ወደ መሬት በማውረድ በተግባር የምታሳይ ታላቅ ሀገር መሆኗን በግልጽ ያረጋገጠ አኩሪ ተግባር ነው።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ ትንሳኤ ብስራት!!
Aug 2, 2026 509
በሐዊ አጫሉ መግቢያ፡- የኢንዱስትሪ ዘርፍ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬን ከሚወስኑ ዋነኛ የብልፅግና ማረጋገጫ ምሰሶዎች መካከል በግምባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ዘርፉ ምርትን ከማሳደግ ባሻገር የሥራ ዕድል ፈጠራን፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና የሀገር ውስጥ ምርታማነትን የሚያፋጥን የልማት ሞተር ነው። ኢትዮጵያም ከግብርና መሠረት የተነሳ ኢኮኖሚዋን ወደ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ሁሉን አቀፍ የምርት ሥርዓት ለማሸጋገር ከምታደርገው ጥረት መካከል ኢንዱስትሪውን በቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶነት በማካተት እየሰራችበት ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና ቴክኖሎጂ አምስት ዐበይት የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት ምሰሶዎች ተመሥርቶ እየተመራ ይገኛል። ከእነዚህ ውስጥ ኢንዱስትሪው የምርት አቅምን በማሳደግ የግብርና ምርቶችን ወደ ተጨማሪ እሴት በመቀየርና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ፋይዳ እያስገኘ ነው። ይህንን ሽግግር እውን ለማድረግ የምርት አቅምን ማሳደግ፣ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር፣ የአቅርቦት ሰንሰለትን ማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና የሰው ኃይል ልማት ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ የቀድሞ ገጽታ፤ ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ለውጥ መንገድ!! በቀደሙት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተለያዩ ዕድሎችንና ፈተናዎችን በማስተናገድ በርካታ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል። ሀገሪቱን ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር በተደረጉ ጥረቶች የተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተገንብተዋል። እነዚህ ፓርኮችም በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳና የቆዳ ውጤቶች እንዲሁም በግብርና ምርት ማቀነባበር ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የተሞከረበት ወሳኝ ምዕራፍ እንደነበር ይታወሳል። ይሁን እንጂ ይህ ጉዞ በበቂ መሠረተ ልማት፣ በተሟላ የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና በተቀናጀ የምርት ሰንሰለት እጥረት ምክንያት በበርካታ ፈተናዎች ለመውደቅ ተገዶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ውስንነት፣ ዕውቅትና ክህሎትን የተሰላበሰ የሰው ኃይል አለመኖር፣ የፋይናንስ እጥረት፣ ውስብስብና አስቸጋሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትና የገበያ ትስስር እጥረት የዘርፉን እድገት ገድበው የነበሩ ሁነኛ ተግዳሮቶች ናቸው። ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ምርታማነት፤ የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የለውጥ ፍኖት!! ባለፉት ዓመታት በኢንዱስትሪ ዘርፉ የተስተዋሉ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታትና የሀገሪቱን የማምረት አቅም ለማሳደግ አዳዲስ የለውጥ አቅጣጫዎች ተነድፈው ተተግበረዋል። በተለይም ኢንዱስትሪን ከተለመደው የምርት ሥርዓት በማሻገር ወደ ተወዳዳሪ ዘመናዊና ውጤታማ የማምረቻ ማዕከል ለመቀየር የተለያዩ የፖሊሲማሻሻያዎች ተደርገዋል። የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ፣ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን ማስፋት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን፣ የሰው ኃይል አቅምን ማሳደግና የግብርና-ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር በዘርፉ የተወሰዱ ሁነኛ የለውጥ እርምጃዎች ናቸው። በዚህም የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት በማጎልበት ከሀገር ውስጥ ገበያ እስከ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ድረስ ውጤት እያስገኘ ነው። የግል ባለሃብቱ ሚና፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሞተር!! የኢንዱስትሪ ልማት በመንግሥት ጥረት ብቻ የሚሳካ አይደለም። የግል ዘርፉ በካፒታል፣ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂና በአስተዳደር ብቃት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ለዘርፉ ዕድገት የማይተካ ሚና አለው። በዚህ ረገድ የግል ባለሃብቱ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ዋና አጋር እንዲሆን የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተሻሽለው እየተሰራባቸው ይገኛል። ይህም የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት በማሻሻል፣ የንግድ ሥራ ሂደቶችን በማቀላጠፍ፣ የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋትና የምርት አቅምን በማሳደግ የግሉን ዘርፉ የምርታማነት አቅም እያጎለበተ ነው። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ የትንሳኤ ብስራት!! በሀገራችን የኢኮኖሚ አቅጣጫ ውስጥ የምርትና አገልግሎት አሰጣጥን በማቀናጀት አዲስ ምዕራፍ ከከፈቱ ዐበይት ሀገራዊ መርሃ-ግብሮች መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተጠቃሽ ነው። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ የማምረት ባህልን በማሳደግ ዘርፉ ወደ አዲስ የልማት ምዕራፍ የሚሸጋገርበት ሁነኛ ዕድልን ፈጥሯል። ንቅናቄው የማምረት አቅምን በማሳደግ ሥራ ያቆሙ ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ መመለስ፣ የአምራቾችን ችግሮች በፍጥነት መፍታትና አዳዲስ ባለሃብቶችን ወደ ዘርፉ በመሳብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤ እያበረከተም ይገኛል። በዚህ ሂደት በፋይናንስ፣ በግብዓት አቅርቦት፣ በውጭ ምንዛሬና በተቋማዊ ቅንጅት ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎች የአምራች ዘርፉን የምርታማነት አቅም በማጎልበት ጉልህ ሚና ተጫውቷል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲያንሰራራ በማድረግ የምርታማነት አብዮት እንዲቀጣጠል እያደረገ ይገኛል። የንቅናቄው ዋና ዓላማ በአምራች ዘርፉ የነበሩ ማነቆዎችን በመፍታት የኢትዮጵያን የማምረት አቅም ማሳደግ ነው። ይህም ሥራ ያቆሙ ወይም በአቅማቸው ልክ ያልሠሩ ፋብሪካዎችን ወደ ሙሉ ምርት በመመለስ የአምራቾችን ችግር በተቀናጀ መንገድ መፍታት፣ የፋይናንስና የግብዓት ተደራሽነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጓል። በዚህ ሂደት የማምረቻ ዘርፉ በአዲስ የሥራ ባህል፣ በተቋማዊ ቅንጅትና በፈጣን ውሳኔ አሰጣጥ እየተመራ መሆኑ የለውጡን ፍጥነት እያሳደገው ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ተደራሽነትን ማሻሻልና የምርት ጥራትን ማረጋገጥ የኢንዱስትሪው ትንሳኤ ዋና ማሳያዎች ናቸው። ለአብነትም፡- የፋይናንስ አቅምና የብድር አቅርቦት ማሻሻል፡- የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዋነኛ እንቅፋት የሆነውን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ በተደረገው ርብርብ፣ የብድር አቅም ቀደም ሲል ከነበረበት 40 ቢሊዮን ብር ወደ 115 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ለአምራቾች ሰፊ የካፒታል አቅም መፍጠር ተችሏል። የውጭ ምንዛሬ ግኝትና የግብዓት ድጋፍ ማደግ፡- ንቅናቄው ከመጀመሩ በፊት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ይቀርብ የነበረው የውጭ ምንዛሬ መጠን አሁን ላይ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንዲደርስ ተደርጓል። ይህም ፋብሪካዎች ከአቅማቸው በታች እንዲሠሩ ያስገድድ የነበረውን የምርት ውስንነት በከፍተኛ ደረጃ አቃሎታል። የምርት ዕድገት፣ ተኪ ምርትና የኤክስፖርት አፈጻጸም፡- ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ረገድ ከነበረበት 348 ሚሊዮን ዶላር ወደ 5.9 ቢሊዮን ዶላር በማደግ ግዙፍ ሀገራዊ ድል ተመዝግቧል። እንዲሁም በኤክስፖርት ገበያ የሚገኘው ገቢ ከ385 ሚሊዮን ዶላር ወደ 607 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ማለት ችሏል። ተቋማዊ ቅንጅትና አዲስ የሥራ ባህል ማዳበር፡- በክልሎችና በፌዴራል ተቋማት መካከል የነበረውን የቢሮክራሲ ጫና በመቀነስ ፈጣን ውሳኔዎች እንዲሰጡ መደረጉ፤ እንዲሁም ህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርትን በኩራት የመጠቀም እና የሀገር ፍቅር ስሜትን ከአምራችነት ጋር የማስተሳሰር ትልቅ ማህበራዊ ንቃተ-ህሊና መገንባት ተችሏል። የወደፊት ተስፋ፤ ኢትዮጵያ አዲሲቷ አፍሪካዊት የኢንዱስትሪ ምርታማነት ተምሳሌት ሀገር!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ በቀጣይ ዓመታት ከተለመደው ማምረት ወደ ዘመናዊ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የምርት ሥርዓት እንዲሸጋገር ይጠበቃል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሜሽን፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና የፈጠራ ሥርዓቶችን ወደ ማምረቻ ዘርፉ ማስገባት የወደፊቱ ትኩረት ይሆናል። በተመሳሳይም ጠንካራ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስር፣ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት፣ ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአህጉራዊ ገበያ ተደራሽነት የሀገሪቱ ቀጣይ የኢንዱስትሪ ግቦች ናቸው። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) የሚፈጥረውን ሰፊ የገበያ ዕድል በመጠቀም ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል እንድትሆን የሚያስችል መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ማጠቃለያ፡- ማምረት፤ የኢትዮጵያ የብልፅግና ቁልፍ መሳሪያ!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ ከፈተና ወደ ዕድል፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል፣ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ተጨማሪ እሴት ያለው ምርት አቅራቢነት በማምራት እመርታዊ ውጤቶችን እያስገኘ ነው። የኢንዱስትሪውን አቅም ማሳደግ ማለት ፋብሪካዎችን ብቻ ማስፋፋት ሳይሆን የሀገርን ምርታማነት፣ የወጣቶችን ዕድል፣ የኢኮኖሚ ነፃነትንና የልማት ዘላቂነትን ማረጋገጥ ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን የዛሬ ልማት ብቻ ሳይሆን የነገውን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚገነባ ሀገራዊ ራዕይ ነው።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ፤ አዲሲቷ የዘመን ተሻጋሪ ዲጂታል ክህሎት የተስፋ አድማስ
Aug 7, 2026 197
በሀሪ መልስ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በወፍ በረር “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ ተጠናቋል። በዛሬው ዕለትም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ አስጀምረናል። ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር፣ እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሠረታዊ ትልሞች ናቸው። እነዚህ ትልሞች እንዲሳኩም በተለይ የሕዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማትን ማስፋት ላይ ትልቅ ሥራ የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ሥራዎች የመደመር መንግሥት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ ናቸው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ዲጅታላይዜሽን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የሚመራ ብሔራዊ የልማትና ዕድገት ፕሮግራም ነው። እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2020 በዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ማዕቀፍ ይፋ የተደረገው ብሔራዊ አጀንዳ በዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂም ቁልፍ ጉዳይ ሆኖ ተይዟል። ግቡም ሁሉንም ተቋማት በኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ በማስተሳሰር በኢትዮጵያ ፈጣን የዲጅታል ኢኮኖሚ ሽግግር መፍጠር ነው። ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት፣ የኢንተርኔትና የዲጅታል ትስስርን ማስፋፋት፣ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎትን ማላቅ፣ ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ የጤና አጠባበቅና የትምህርት ሥርዓትን ማሻሻል፣ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የዲጅታል ኢኮኖሚ መገንባት፣ በኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ እንዲሁም በኢኖቬሽን የሥራ ዕድል መፍጠር እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማትን መደገፍ የዲጅታላይዜሽን መሠረቶች ናቸው። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የዲጅታል ኢኮኖሚ መሠረት ጥሏል። በመንግሥት ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥን በዲጅታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል፤ ተጠያቂነት የሰፈነበት የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋትም ብልሹ አሠራርን ለመከላከል የሚያስችል መሠረት ጥሏል። የዲጅታል ማንነትን በማስፋፋት ዜጎች አገልግሎቶችን በኤሌክትሮኒክ ሥርዓት ማግኘት እንዲችሉ ያስቻለ ሲሆን፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን፣ ቅንጅትንና ተደራሽነትንም አሳድጓል። ቀደም ሲል ዜጎች ዲጅታል ማንነት መጠቀም በማይችሉበት ወቅት በርካታ የወረቀት ሰነዶችን ከማቅረብ ጀምሮ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትን በመዳረስ ረጅም ጊዜና ጉልበት ያጠፉ ነበር። አሁን ግን ሁኔታው ተለውጧል። በወረቀት አልባ ሥርዓት ፈጣንና ፍትሐዊ የመንግሥት አገልግሎት ማግኘት የሚቻልበት የዲጅታል ምህዳር ተፈጥሯል፤ የዜጎች እንግልት ቀንሷል፤ ወረፋና ጥበቃም ተረት ሆኗል። የዲጅታል ክፍያ ሥርዓትም በኢትዮጵያውያን ዘንድ እንደዕለት ተዕለት አጠቃቀም ቀላልና የተለመደ እየሆነ መጥቷል። የቴሌኮም መሠረተ ልማትን የማስፋፋት ሥራም ተጠናክሯል፤ የዲጅታል ክህሎት በተለይም በወጣቶች ዘንድ አዲስ የእውቀትና የተወዳዳሪነት መሣሪያ ሆኗል። ለዲጅታል መሠረተ ልማት መስፋፋት ቁልፍ የሆኑ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፎችም ተፈጥረዋል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ የዲጅታል ኢኮኖሚ ሽግግር መሠረት ጥሏል፤ የኢትዮጵያን መጪ ጊዜ በተስፋ መመልከት የሚያስችል አጉሊ መነጽር አቅርቧል። በዲጅታል ክፍያዎች የታገዘ የጥሬ ገንዘብ አልባ ግብይትም የሀገሪቱን አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እያዘመነ ይገኛል። ጥሬ ገንዘብ በእጅ የመያዝ ልማድ መቀነሱ የገንዘብ ማተሚያና ማጓጓዣ ወጪን ቀንሷል፤ የገንዘብ ዝውውርን ግልጽና ፈጣን በማድረግም ሕገወጥ አሠራሮችንና ሙስናን ለመከላከል አስችሏል። ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ጥበቃ ከተደረገለት የፋይናንስ ሥርዓት ጋር ሲቀናጅም፣ ሕዝቡ በዲጅታል ክፍያዎች ላይ ያለው መተማመን እንዲጎለብት ያደርጋል፤ የሀገሪቱንም የዲጅታል ሽግግር ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል። ይህም ለዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሠረት ጥሏል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030፤ የሽግግሩ ቀጣይ ምዕራፍ የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የመንግሥትና የግል ዘርፍ አጋርነትን በማጠናከር፣ የኤሌክትሮኒክ የመንግሥት አገልግሎቶችን ፍጥነት፣ ተደራሽነትና ግልጽነት ለማሳደግ ያለመ ነው። ይህም የመንግሥትን ወጪ ለመቀነስና የአገልግሎት ብቃትን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬትም በኢኮኖሚ፣ በትምህርትና በአገልግሎት ዘርፎች አዎንታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። የሀገሪቱ የዲጅታል ሽግግር በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ላይ በተመሠረተው የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ላይ የተቃኘ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስትራቴጂ ማስጀመሪያው ወቅት፦ ስትራቴጂው በከተማም ሆነ በገጠር የዲጅታል ሥርዓትን በማስረጽ የዲጅታል ኢኮኖሚን እውን የምናደርግበት ነው ብለዋል። ቁሳዊ ዕድገት የሚጀምረው የሰው ኃይል አቅምን በመገንባት እንደሆነ ጠቅሰው፣ ወጣቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ፣ የፈጠራ ባለቤቶችና ሥራ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ በዲጅታል ክህሎት ማስታጠቅ እንደሚገባ አጽንዖት ሰጥተዋል። የዲጅታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂያዊ ግቦች ኢትዮጵያ የብሮድባንድና ኢንተርኔት ተደራሽነትን በመላ ሀገሪቱ በመዘርጋት፣ የዜጎችና ተቋማትን የዲጅታል ክህሎት በማሳደግ፣ እንደ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ስታርትአፖችን በቴክኖሎጂ በማዘመን የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትና ንግድን መሳብ፣ እንዲሁም አካታች የዲጅታል ኢኮኖሚ መገንባት ናቸው። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የመንግሥት የዲጅታል አገልግሎት ማስፋፊያ፣ የቴሌኮም ሪፎርም፣ ዲጅታል ክፍያ፣ ብሔራዊ የዲጅታል መታወቂያ/ፋይዳ፣ እንዲሁም በሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ ዲጅታል የሕዝብ መሠረተ ልማት፣ የሳይበር ደህንነትና ብሔራዊ የዲጅታል አካታችነትን መርህ ያደረገውን የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አዋልዷል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጅታል ሽግግር ስትራቴጂ ነው። ከዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬት የተቀዳ ታላቅ የመሆን ህልም ሥጋ ለብሶ የታየበት ግልጽ ፍኖተ ካርታም ነው። የዲጅታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም፣ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2030 ቀልጣፋ የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ፣ የአስተዳደር ሥርዓትን በማጠናከር አገልግሎትን ማሻሻል፣ በዲጅታል ቴክኖሎጂ የበቃ ማኅበረሰብ በመፍጠር ሀገርን ማበልጸግ፣ ለነገ ዛሬ የሚኖር አደራና ዛሬ የነገ ስንቅ ሆኖ በግልጽ ሰፍሯል። የኢትዮጵያ የዲጅታል ሽግግር ግብ አንድ ነው፤ አካታችና ዘላቂ ዲጅታል ኢኮኖሚ መገንባት፣ በዋጋ ተመጣጣኝና ተደራሽ የኢንተርኔትና የኮሙኒኬሽን አገልግሎትን ማስፋት፣ በዲጅታል ኢኮኖሚ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የመረጃ አስተዳደርና የሳይበር ደህንነት ጥበቃን ሕልው ማድረግ፣ የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትን መጨመር፣ ዲጅታል ክህሎትና ኢኖቬሽንን ማሳለጥ ነው። ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ /ፋይዳ/፤ የዲጅታል ሽግግር መልህቅ ''በቅርብ ዓመታት ውስጥ፣ ዲጅታል ማንነት ተስፋ ሰጪ ከሆነው ፈጠራ ወደ ዲጅታል ሽግግር መሠረታዊ ምሰሶ ተሻሽሏል። ከአሁን በኋላ አማራጭ ሳይሆን፣ ሰዎችን ከአገልግሎቶች፣ ከማኅበረሰቦች፣ ከተቋማት እና ከመንግሥታት ጋር የሚያገናኝ አስፈላጊ መሠረተ ልማት ነው። ፋይዳ ካርድ ብቻ አይደለም። የግለሰቦችን የግል መረጃ ምሥጢራዊነት በመጠበቅና አስፈላጊ የሆነውን መረጃ ብቻ በማጋራት ማንነትን የሚያረጋግጥ ልዩ መለያ ቁጥር ነው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ /ፋይዳ/፤ የዲጅታል ሽግግር መልህቅ የዲጅታል ብሔራዊ መታወቂያ /ፋይዳ/ (National Digital ID) በኢትዮጵያ ሥራ የጀመረው እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2023 ነበር። ምንም እንኳን የፕሮጀክቱ ዝግጅትና ሕጋዊ መሠረት ቀደም ብሎ የተጀመረ ቢሆንም፣ በአዋጅ ቁጥር 1284/2015 በሕግ ተቋቁሟል። እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር ከ2019 እስከ 2020 ባለው ጊዜም ፋይዳ በዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ አካል ሆነ። ከዚያም ምዝገባው በመላ ኢትዮጵያ ተስፋፍቶ፣ ከመንግሥት አገልግሎቶች፣ ከባንኮች፣ ከዲጅታል ክፍያ ሥርዓት እና ከመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት ጋር ተሳስሯል። በኢትዮጵያ እያንዳንዱን ነዋሪ የአንድ ልዩ የዲጅታል መለያ ባለቤት ማድረግ የፕሮጀክቱ ዋነኛ ግብ ነው። ይህም የመንግሥትና የግል አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘት የሚቻልበትን ሥርዓት ለመዘርጋት፣ የማንነት ማጭበርበርና ድርብ ምዝገባን ለማስቀረት እንዲሁም የኢትዮጵያን ዲጅታል ኢኮኖሚ ለመደገፍ ያስችላል። ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የነዋሪዎችን የባዮሜትሪክና ዲሞግራፊክ መረጃ በመሰብሰብ፣ ''አንድ ሰው፣ አንድ ማንነት” በሚል መርህ እያንዳንዱን ሰው ልዩ በሆነ ሁኔታ መለየት የሚያስችል ሥርዓት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ስለፋይዳ አስፈላጊነት ሲናገሩ፣ “ፋይዳ በአማርኛ፣ በኦሮሚኛ፣ በትግርኛ፣ በሱማሊኛ፣ በአፋርኛ እንዲሁም በአረብኛ፣ በሂንዱኛና በተርኪሽ ቋንቋዎች ፋይዳ ነው። … ዲጅታል መታወቂያ /ፋይዳ/ በጣም ጠቃሚ ነገር ነው፤ ከሕዳሴ የሚያንስ አይደለም። እንደ ሀገር ዲጅታል መታወቂያ ብንሠራ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርት በሰባት ፐርሰንት ይጨምራል። ፋይዳ የመተማመኛ ሥርዓት ነው…” በማለት የፋይዳን መልከ ብዙ ፋይዳ ገልጸዋል። ፋይዳ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና የዲጅታል ኢኮኖሚ ሽግግሩን ለማሳለጥ ቁልፍ መሣሪያ መሆኑንም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ከ150 በላይ ተቋማት ጋር ተሳስሯል። ከ48 ሚሊዮን በላይ ዜጎችም ተመዝግበዋል። እስከ 2020 ዓ.ም ድረስ የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ወደ 115 ሚሊዮን ለማድረስ ጉዞው ቀጥሏል። በዚህም በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ወደ መደበኛ የፋይናንስ ሥርዓት ለማስገባት እያገዘ ይገኛል። መንገዶች ሁሉ ኢትዮጵያን ወደ ዲጅታል ሽግግር በሚወስዱበት ሀዲድ፣ ፋይዳ መሪ ተዋናይ ሆኖ ይቀጥላል። ዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት እንዲያገኙ፣ የባንክና የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲጠቀሙ የሚያስችል የቴክኖሎጂ ምህዳር ይፈጥራል። መንግሥትም ማጭበርበርን ለመከላከል፣ በተቋማት መካከል ግልጽና የተቀናጀ ትብብርን ለመዘርጋት እና የተሻለ የሕዝብ አገልግሎት የሚሰጥበትን ዕድል እውን ለማድረግ ፋይዳን ይጠቀማል። የቢዝነስ አንቀሳቃሾችም ዲጅታል ግብይትን፣ ፋይናንስንና ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሥራቸውን የበለጠ ቀልጣፋና ተደራሽ ማድረግ ይችላሉ። በአጭሩ፣ ፋይዳ ''ሁሉ በእጄ፣ ሁሉ በደጄ” የሚለውን የዲጅታል ኢኮኖሚ ራዕይ እውን ለማድረግ የሚያግዝ ቁልፍ መሠረተ ልማት ነው። መሶብ፤ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት የጊዜና የቦታ ልጓም ''ሀገራዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሠረታዊ የሆነ የባህል ለውጥ ያስፈልጋል። ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን እንገኛለን። መሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትን ተግባራዊ ማድረግ የጀመርነው በቅርብ ጊዜ ቢሆንም፣ በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል። ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያመላክታል።”ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት፤ የጊዜና የቦታ ልጓም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 12 የፌዴራል ተቋማት 40 የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር እንዲሰጡ በማድረግ ሚያዚያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቆ ሥራ ጀምሯል። እነሆ ማዕከሉ የተቋማትንና የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ቁጥር እያሳደገ የኢትዮጵያን የዲጅታል ሽግግር ፍኖት እየቀረጸ ይገኛል። ዜጎችም በዲጅታል መሠረተ ልማት የተደገፈ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል። ከዚህ በፊት የዜጎችን ጊዜ የሚያባክኑ ረጅም ወረፋዎች፣ የተለያዩ ቢሮዎችን ደጋግሞ መጎብኘት፣ “ሰነድ ይጎድላል፣ ኮፒ አድርገህ አምጣ” የሚሉ የወረቀት ሥራዎች በአዲሱ የአገልግሎት ሥርዓት እየተቀየሩ ነው። አዲስ የአገልግሎት አድማስ የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ220 በላይ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ሕንፃ ሥር በማቅረብ የዜጎችን የጊዜና የቦታ ጫና ቀንሷል። ከቀበሌ መታወቂያ ማውጣት ጀምሮ እስከ ከፍተኛ የንግድና የጉምሩክ አገልግሎቶች ድረስ በቀላሉ ማግኘት የሚቻልበት ምቹ ምህዳር ተፈጥሯል። ፈጣንነት፣ ቅልጥፍና፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና መርሆዎች ሆነዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ባስጀመሩበት ወቅት፤ ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፣ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ብለዋል። የዲጅታል አገልግሎት የዜጎችን ጊዜና ጉልበት የሚቆጥብ አዲስ የአስተዳደር ባህል መሆኑን ገልጸዋል። በአጠቃላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የወረቀት እና የወረፋ ዘመንን በመቀየር ዜጋን ማዕከል ያደረገ፣ ቀልጣፋና ዲጅታል የሆነ የአገልግሎት ሥርዓት እየገነባ ያለ የለውጥ ምሳሌ ሆኗል። የ5-ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ፤ የዲጅታል ክህሎት ማበልጸጊያ መድረክ በዲጅታል ዘመን የሰው ኃይል አቅም የሀገራት የዕድገት መሰረት እሆነ ነው። ኢትዮጵያም የወጣቶቿን የፈጠራና የቴክኖሎጂ አቅም ለማሳደግ ትልቅ የዲጅታል ክህሎት ማበልጸጊያ መርሃ ግብር ጀምራለች። የ5-ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢንሼቲቭ የወጣቱን ትውልድ የፕሮግራሚንግ፣ የሶፍትዌር ልማት፣ የፈጠራ ሥራና የዲጅታል ቴክኖሎጂ አቅም ለማጎልበት የተቀረፀ ሀገራዊ አጀንዳ ነው። መርሃ ግብሩ ወጣቶችን የዲጅታል ኢኮኖሚ ተሳታፊዎች ብቻ ሳይሆኑ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎችና የሀገር በቀል መፍትሔ አበልጻጊዎች ለማድረግ ያለመ ነው። ''ይህም ኢትዮጵያ በዓለም የዲጅታል ውድድር ውስጥ የምትኖራትን ሚና ለማሳደግ፣ የቴክኖሎጂ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና በአፍሪካ የፈጠራ ማዕከል ለመሆን የሚያግዝ የወደፊት ራዕይ ነው። ኢትዮጵያ ወደፊት የሚያልሙ አሳቢ ወጣት ዜጎቿ ተስፋ አላት። የ‘አምስት ሚሊዮን ኮደርስ’ መርሃ ግብር ታላቅ እድል ነው። አምስት ሚሊዮኖቹ ኮደሮች ሀገር በቀል መፍትሔዎችን የሚሰጡ ብቻ ሳይሆኑ፣ ለአህጉራችን የተስፋ ብርሃን የሚፈነጥቁ ናቸው።''ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአጠቃላይ 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ የዲጅታል ክህሎትን ከመገንባት ባሻገር፣ የወጣቱን የፈጠራ ኃይል ወደ ሀገራዊ የዕድገት ሞተር ለመቀየር የተቀረፀ የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ዋነኛ መሠረት ነው። 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢንሼቲቭ፤ የዲጅታል ክህሎት ማበልጸጊያና የወጣቱ የወደፊት አቅም በፍጥነት በሚለዋወጠው የዲጅታል ዓለም ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት መያዝ አማራጭ ሳይሆን የዘመኑ ግዴታ ሆኗል። ዛሬ ላይ በመትጋት ነገን ማልማት የእያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት ሲሆን፣ የሀገር ዕድገትም የሰው ኃይል አቅም ግንባታ ላይ ይመሰረታል። መንግሥት የበለጸገችና በቴክኖሎጂ የተደገፈች ኢትዮጵያን ለመገንባት ከለያቸው አምስት ቁልፍ የትኩረት መስኮች መካከል አይ.ሲ.ቲ (ICT) አንዱ ነው። በዚህ ራዕይ መሠረት የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማሳለጥ ሦስት ቁልፍ የዲጅታል ሽግግር ማስፈጸሚያዎች ተግባራዊ ሆነዋል። እነሱም መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት፣ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ (ፋይዳ) እና 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ ናቸው። የወጣቱን የዲጅታል አቅም የሚገነባ ታላቅ ኢንሼቲቭ 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ በኢትዮጵያና በተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ትብብር ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ በሦስት ዓመታት ውስጥ 5 ሚሊዮን ወጣቶችን በዲጅታል ክህሎት ለማሰልጠን የተቀረጸ ፕሮግራም ነው። ፕሮግራሚንግ (Programming)፣ የመረጃ ትንተና (Data Analysis)፣ የአንድሮይድ ልማት (Android Development) እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት መሠረቶች (Artificial Intelligence Fundamentals) የሥልጠናው ዋና የክህሎት ዘርፎች ናቸው። ኢንሼቲቩ የተያዘለትን ግብ በፍጥነት እያሳካ ይገኛል። ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ከ5 ሚሊዮን በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበዋል፤ ቁጥሩን እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም 7 ሚሊዮን ለማድረስ ዕቅድ ተይዟል። ይህም የወጣቶችን ለሥራ ዓለም ተፈላጊነት ከማሳደግ ባሻገር፣ የሀገሪቱን የዲጅታል የሰው ኃይል ልማት ያጠናክራል። በመንግሥት ተቋማት የሶፍትዌር ልማትና የዲጅታል ሽግግር ሥራዎችን የሚያሳልጡ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችንም ያፈራል። በኢንሼቲቩ አማካኝነት 1 ሚሊዮን የዲጅታል የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ከዲጅታል ምርቶች ወጪ ንግድ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት የተቀመጠው ዕቅድ የፕሮግራሙን ሀገራዊ ፋይዳ ያመላክታል። የወጣቶች የፈጠራ ኃይል የኢትዮጵያ የዲጅታል ተስፋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየትኛውም የትምህርትና የዕውቀት ደረጃ ላይ ያሉ ወጣቶች የአምስት ሚሊዮን ኮደሮች ፕሮጀክትን በመጠቀም ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ ጥሪ አቅርበዋል። የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከላት፣ አሰልጣኞችና ዩኒቨርሲቲዎችም የፕሮግራሙን ስኬት ለማስፋት የሚያደርጉት አስተዋፅኦ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጅታል ሽግግር ሦስቱ ምሰሶዎች በጥቅሉ 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ፣ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ (ፋይዳ) እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የኢትዮጵያን የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያስፈጽሙ ተያያዥ ምሰሶዎች ናቸው። ኮደርስ የዲጅታል ኢኮኖሚውን የሚገነባና የሚያስፋፋ የሰው ኃይል ያበረክታሉ፤ ፋይዳ ደግሞ የደህንነቱ የተጠበቀ የዲጅታል ማንነት ሥርዓት ይፈጥራል፤ መሶብም በአንድ ጣሪያ ሥር ፈጣንና ግልጽ የህዝብ አገልግሎት ያሳልጣል። ከዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ራዕይ ጋር ተጣምረው እነዚህ ሦስት የለውጥ ምሰሶዎች ኢትዮጵያን ወደ አካታች፣ ዘላቂና ተወዳዳሪ የዲጅታል ኢኮኖሚ ለማሸጋገር የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው። ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የኢትዮጵያ ተሻጋሪ ህልሞች መመልከቻ በኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እ.ኤ.አ. በ2020 የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በመመስረት ተቋማዊ መሠረት የያዘ የልማት አቅጣጫ ሆኗል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፖሊሲና ሕጋዊ ማዕቀፎች በመዘርጋታቸው ዘርፉ በተደራጀ አሠራር እንዲመራ ተደርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጎበኙበት ወቅት፣ ሰው የጠራ ራዕይ ካለው፣ በከፍተኛ ዲሲፕሊን የሚሠራ ከሆነ ያሰበውን ማሳካት እንደሚችል፤ ኢትዮጵያ ብቃት ያላት ሀገር መሆኗን በመግለጽ የዘርፉን ሀገራዊ ጠቀሜታ አስረድተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሀገር ውስጥ የፈጠራ አቅምን በማበረታታት ዘርፈ ብዙ ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች እንዲመነጩ እያደረገ ይገኛል። በግብርና፣ በጤና፣ በፋይናንስ፣ በደህንነትና በአገልግሎት ዘርፎች የሚያገለግሉ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መፍትሔዎች በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች መፍጠር ጀምረዋል። በአማርኛ፣ ኦሮምኛና ትግርኛ ቋንቋዎች የተዘጋጁ የጽሑፍና የድምፅ ማቀናበሪያ ቴክኖሎጂዎች (NLP)፣ በጤና ዘርፍ የጡት ካንሰር፣ የስኳር በሽታና የሳንባ በሽታዎችን በምስል ምርመራ ቀድመው ለመለየት የሚያግዙ የAI መፍትሔዎች፣ በግብርና ዘርፍ የቡናና የሰብል በሽታዎችን የሚለዩ መተግበሪያዎች እየተስፋፉ ነው። በተጨማሪም ለከተማ ደህንነት፣ ለፖሊስ ሥራ፣ ለጉምሩክ ቁጥጥርና ለፋይናንስ ተቋማት የሚያገለግሉ ቻትቦቶችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች በመስኩ እየተተገበሩ ይገኛሉ። የታዳጊዎች የሰመር ካምፕ የAI ስልጠናዎችም የወደፊቱን የቴክኖሎጂ ባለሙያ ትውልድ ለማፍራት እያገዙ ናቸው። የኢትዮጵያ የዲጅታል ሽግግርና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ጉዞ በሀገር ድንበር የማይገደብ፣ የአፍሪካን ዲጂታል ሽግግር ታሳቢ ያደረገ አህጉራዊ ራዕይ ነው። ለዚህም ኢትዮጵያ የፓን አፍሪካ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኮንፈረንስን በማዘጋጀት አፍሪካ በዲጂታል ሽግግር፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ ትብብር እንድትጠናከር ያላትን ራዕይ አሳይታለች። በአፍሪካ ቀዳሚ ከሚሆኑ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከላት አንዱ የሆነው የAI ዩኒቨርሲቲ ግንባታም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ለማሳካት፣ የአፍሪካን የቴክኖሎጂና የፈጠራ አቅም ለማሳደግ የተያዘ ተሻጋሪ ራዕይ ነው። በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ለኢትዮጵያ የወደፊት የዕውቀት ኢኮኖሚ፣ የፈጠራ አቅምና የዲጂታል ሉዓላዊነት መሠረት እየሆነ የሚሄድ ተሻጋሪ መሣሪያ ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር፤ የዲጅታል ሉዓላዊነት እና ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ዘብ የዓለም የዲጅታላይዜሽን ሽግግር በብርሃን ፍጥነት እየተስፋፋ ባለበት ዘመን፣ ቴክኖሎጂን መጠቀም ብቻ ሳይሆን የዲጅታል መሠረተ ልማቶችን ከሳይበር ስጋቶች መጠበቅ የሀገራት ቁልፍ ተግባር ሆኗል። በዚህ የቴክኖሎጂ ውድድር ዓለም የመረጃ ደህንነት ከቴክኒክ ጉዳይ ባለፈ የሀገር ሉዓላዊነትና ህልውና ጉዳይ እየሆነ መጥቷል። ኢትዮጵያም የዘግይቶ መግባት ጥቅም (Latecomer Advantage) በመጠቀም የዲጅታል ሽግግሯን በዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ላይ ለመገንባት እየሠራች ትገኛለች። ይህንን የዲጅታል ጉዞ አስተማማኝ ለማድረግና የሀገሪቱን የመረጃ ሀብት ለመጠበቅ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ወሳኝ ሚና እየተወጣ ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የኢትዮጵያን የኢንፎርሜሽን ሥርዓቶችና ቁልፍ የመረጃ መሠረተ ልማቶች ከሳይበር ጥቃት የመጠበቅ፣ የመረጃ ደህንነትን የማረጋገጥና ብሔራዊ ጥቅሞችን የማስከበር ተልዕኮ ተሰጥቶታል። የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ፣ የደህንነት ኦፕሬሽን ማዕከላት (Security Operation Centers) እና የዲጅታል ፎረንሲክ ላቦራቶሪዎች ግንባታ ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። እነዚህ ዘመናዊ የዲጅታል ደህንነት መሠረተ ልማቶች እንደ ባንክ፣ ቴሌኮም፣ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ቁልፍ ሀገራዊ ተቋማትን ከተወሳሰቡ የሳይበር ጥቃቶች አስቀድሞ ለመከላከል፣ አደጋ ቢከሰትም ፈጣን ሕጋዊና ቴክኒካዊ ምላሽ ለመስጠት ያስችላሉ። የመረጃ ደህንነት፤ የዲጅታል ኢኮኖሚ መሠረት በዛሬው ዓለም መረጃ (Data) እንደ አንዱ ዋና ሀብት በመቆጠሩ፣ የዜጎችን ግላዊ መረጃ፣ የፋይናንስ ግብይቶችንና የመንግሥት ሚስጥራዊ መረጃዎችን በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ የዲጅታል ሉዓላዊነት ዋና መሠረት ሆኗል። ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ሥርዓት መኖሩ ዜጎች በዲጅታል አገልግሎቶች ላይ እምነት እንዲያሳድሩ፣ የግልና የውጭ ባለሀብቶችም በኢትዮጵያ የዲጅታል ኢኮኖሚ ላይ የተሻለ እምነት እንዲኖራቸው ያደርጋል። በዚህም የሳይበር ደህንነት የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ስኬትን የሚደግፍ ዋና የጥበቃ መሠረት ሆኖ ይቀጥላል። ማጠቃለያ፡ ዲጂታል ኢትዮጵያ፤ የወደፊት ተወዳዳሪነት መሠረት የኢትዮጵያ የዲጂታል ሽግግር ጉዞ ከፖሊሲ ቀረጻ እስከ ተግባራዊ የዲጂታል መሠረተ ልማት ዝርጋታ በፍጥነት እየተሻገረ ይገኛል። ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሚመራ ሲሆን፣ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ /ፋይዳ፣ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት፣ አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ልማትና የሳይበር ደህንነት ሥርዓት ዋና ዋና የሽግግሩ ምሰሶዎች ሆነዋል። ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ /ፋይዳ የዜጎችን ዲጂታል ማንነት በማረጋገጥ ለዲጂታል አገልግሎቶች መሠረት ሲሆን፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሕዝብ አገልግሎትን በፍጥነት፣ በቅልጥፍናና በግልጽነት ለማቅረብ አዲስ የአሠራር ባህል እየገነባ ነው። አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ደግሞ ለዲጂታል ኢኮኖሚው የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል በማፍራት የቴክኖሎጂ ፈጠራና የዲጂታል ሥራ ዕድል እድገትን ያፋጥናል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዩኒቨርሲቲና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ልማት ተቋማት የወደፊቱን የእውቀትና የፈጠራ አቅም ለመገንባት ወሳኝ ሚና ይኖራቸዋል። በተመሳሳይም የሳይበር ደህንነት ሥርዓት የዲጂታል ኢኮኖሚውን ከስጋቶች የሚጠብቅ፣ የመረጃ ደህንነትንና የሀገር ዲጂታል ሉዓላዊነትን የሚያስከብር ጠንካራ ጋሻ ሆኖ ይቀጥላል። በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽንና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፎች ኢትዮጵያ እየወሰደች ያለችው መዋቅራዊ እርምጃ የአገር ውስጥ አገልግሎቶችን ከማዘመንና የዜጎችን ኑሮ ከማቅለል ባለፈ፣ ሀገሪቱን በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ፣ አካታችና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ኢኮኖሚ ባለቤት ለማድረግ የሚያግዝ ነው። ኢትዮጵያ አዲስ የተስፋ አድማስ፡- '’ኢትዮጵያዊነት ያስተማረን ትልቁ እውነት፤ በጊዜያዊ ፈተናዎች ተሸንፎ መውደቅ ሳይሆን፣ ችግሮችን ወደ ዕድል፣ ፈተናዎችንም ወደ ስኬት መለወጥና ድልን መቀዳጀት ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ያስመዘገባቸው ውጤቶች ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ቀጣይ የልህቀት ጉዞ ጠንካራ መነሻና መሠረት ይሆናሉ። በመሆኑም ኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታዋን ለማፋጠን በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተጀመሩ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተቀናጀ መንገድ በጋራ ገቢራዊ ማድረግ ይጠበቅባታል። ዲጂታል ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የእውቀት፣ የፈጠራና የተወዳዳሪነት ሀገራዊ መሠረት ነው።
የመደመር ፍሬ፡አረንጓዴዋ ኢትዮጵያ
Aug 5, 2026 481
በሙሴ መለሰ የመደመር እሳቤ ዋና መሠረቱ እውቀትን፣ጉልበትን፣ሀብትንና አቅምን አስተባብሮ ለአንድ የጋራ ዓላማ በጋራ ማቆምን ያመለክታል። ይህን የሃሳብ ልዕልና በተግባር ፈትሾ ተጨባጭ ውጤት የታየበት ላለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ነው። አረንጓዴ ዐሻራ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም ጅማሮውን አግኝቷል። የአረንጓዴ ዐሻራ ትልቁ ማሳያ የህዝብ ህብረት የታየበት መሆኑ ነው። በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እድሜ፣ ጾታ እና ልዩነት ሳይበግራቸው በነቂስ በመውጣት በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል አኩሪ ታሪክ የሰሩበት ህዝባዊ ንቅናቄ የመደመርን አስተሳሰብ በተግባር ያረጋገጠ ነው። ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ ከተካሄደው የአንድ ጀምበር መርሃ ግብር እንደታየው፣መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያለ ምንም ክፍያ በሙሉ ፈቃደኝነት እና በዝናብ ውስጥ ውሎ ከ805 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ሰርቷል። በአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላው 26 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዜጎች ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ተደምረው ለነገ ልጆቻቸው መሰረት ለመጣል ሲወስኑ ምን ማድረግ እንደሚችሉ ለዓለም ህዝብ ያሳዩበት ህያው አብነት ነው። የመደመር እሳቤ በቃላት ሳይሆን በተጨባጭ ውጤት የሚለካ ነው፤ በዘንድሮው የችግኝ ተከላ ዘመቻ እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ቀሪው 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ ደግሞ በቀጣይ ጊዜያት ይተከላል። በአንድ ወቅት ከ40 በመቶ በላይ የደን ሽፋን የነበራት ኢትዮጵያ ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሃብትና የመሬት አጠቃቀም ምክንያት የደን ሽፋኗ ወደ 3 በመቶ ወርዶ ነበር። አረንጓዴ አሻራ ሀገራዊ የደን ሽፋን ከነበረበት 17.2 ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ በማሳደግ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ችግኝ ተከላው ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ከምግብ ዋስትና እና ከሀገር ኢኮኖሚ ጋርም የተሳሰረ ነው። በፍራፍሬ እንደ አቮካዶ፣ማንጎ እና ቡና ባሉ ምርታማ ችግኞች ላይ በማተኮሩ የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባሻገር፣ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት የምትበለጽግ፣የማትለምን እና ለተቸገሩት የምትደርስ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል የዜጎችን ገቢ የማሳደግ ድርሻ አለው። ኢትዮጵያ ችግኞችን ለጎረቤት ሀገራት በመስጠት ያከናወነቻቸው የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ስራዎች የመደመር እሳቤ ድንበር አቋርጦ ለአህጉራዊ ትስስር እና ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ የሚሆን ድንበር ተሻጋሪ እሴት እንዳለው ያሳያል። ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዋ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ ምክንያት ሆኗል። ይህም የኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረት ዓለም አቀፍ እውቅናን አስገኝቷል። በአጠቃላይ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያን በቀና እሳቤ እና በትብብር በመቆም ተስፋን ለልጆቻቸው መዝራት እንደሚችሉ በተግባር፣በስራና በውጤት ያረጋገጡበት ትልቅ ሀገራዊ ኩራት ነው።
በተቃርኖ የተሞላው ሕገ ወጡ ሕወሓት የጥፋት ጉዞ
Jul 30, 2026 712
የሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን የፖለቲካ ጉዞ በበርካታ መሠረታዊ ተቃርኖዎችና የፖለቲካ ስህተቶች የተሞላ ነው። ቡድኑ በትግል ጊዜም ይሁን ሀገርን በመምራት ባደረገው የፖለቲካ ተሳትፎ ታሪክ ይቅር የማይላቸው ስህተቶችን ፈጽሟል። ከሁሉም በላይ የትግራይን ሕዝብ ለዘመን ተሻጋሪ መከራና ስቃይ ዳርጓል። የወጣቶችን ተስፋ እና ሕልም አጨልሟል። የሕገ ወጡ ቡድን በተቃርኖ የተሞላ ጉዞ በጨረፍታ እንመልከት። ተቃርኖ አንድ፦ የሀገር ገዥነት እና የነጻ አውጪነት መንፈስ ሕገ ወጡ ሕወሓት ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ግንባር ፈጥሮ ሀገር በመራበት ዘመንም ጉዞው በተቃርኖ የተሞላ ነበር። በዚህ የሥልጣን ዘመኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ከአንድነት ይልቅ ልዩነትን፤ ከኅብረት ይልቅ መነጠልን ሥር እንዲሰድ አድርጓል። በስም ደረጃ ሕብረ ብሔራዊ የፌዴራል ሥርዓት እንደሚያራምድ ቢናገርም ለኢትዮጵያውያን የተለያየ የዳቦ ስም በመስጠት እርስ በእርስ እንዲጠራጠሩ በማድረግ የጥላቻ ፖለቲካን አንግሷል። የሕግ የበላይነት እና የሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት በአንዱ ቡድን ላይ የማይተገበር ሌላው ላይ ግን ተግባራዊ እንዲሆን አድርጓል። ከቡድኑ ጋር የጥቅም ትስስር ያላቸው ቡድኖች ለሕግ የማይገዙ፣ ከኮንትሮባንድ እስከ ዓለም አቀፍ ወንጀሎች ውስጥ የሚሳተፉ ነበሩ። ሌላው ጽንፈኛ፣ አክራሪ እና ተስፋፊ ተደርጎ በሽብር እየተወነጀለ በየማረሚያ ቤቱ እንዲንገላታ ተደርጓል። በጥቅሉ ሕገ-መንግሥት እና የፌዴራል ሥርዓትን ለራሱ በሚያመች መልኩ ሲጠቀምበት ቆይቷል። ከዚህም ባለፈ ሕገ ወጡ ቡድን ሀገርን እየመራ እንደ አንድ የክልል ነጻ አውጪ ድርጅት በብሔሮች መካከል ጥርጣሬና ልዩነት እንዲሰፋ የሚያደርጉ የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካዎችንም አንግሷል። ‘እኛ እና እነሱ’ የሚል ፖለቲካን ከማካሄድ ባለፈ ‘ልዩ ኃይል’ በሚል ወታደራዊ አደረጃጀት ፈጥሮ መንግሥት መስሎ ሀገርን የማፍረስ እና የማዳከም ተግባር ውስጥ ተሳትፏል። ተቃርኖ ሁለት፦ ሰሜን እዝን ባጠቃበት ጊዜ ሕገ ወጡ ቡድን ራሱ ያደራጀውን እና ሲያሞካሸው የቆየውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 2013 ዓ.ም. በማጥቃት የተቃርኖ ጉዞውን መቀጠሉን አረጋግጧል። በሀገር መከላከያ ሠራዊት ሰሜን እዝ የትግራይ ሕዝብ ጋሻና መከታ፣ የችግር ጊዜ ደራሽ እና ከሻዕቢያ ተከላካይ ሆኖ ላቡንና ደሙን ገብሯል። ሕገ ወጡ ቡድን የሀገር ሉዓላዊነትና የሕገ-መንግሥት ጠባቂ ነኝ ሲል ቆይቶ፣ ለ20 ዓመታት በትግራይ ሕዝብ ደህንነት ጥበቃ ላይ የነበረውን እና የትግራይ ተወላጆችንም በሠራዊቱ ውስጥ ያቀፈውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት አጥቅቷል። ሴረኛው እና በተቃርኖ የተሞላው ቡድን የማይመርዝና የማይለውጠው መሆኑን ያረጋገጠበትን ድርጊት ፈጽሞ የሀገር ጋሻና መከታን አዋርዷል። ይህ ድርጊት በኢትዮጵያ ዘመናዊ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እጅግ አሳፋሪ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል። የተቃርኖው ውጤት ግን መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ባልተጠበቀ ሁኔታ አንድ ላይ አስተሳሰረ፤ ለሉዓላዊነትና ለግዛት አንድነት የአባቶቹን ታሪክ እንዲደግም ዕድል ፈጠረ። ተቃርኖ ሦስት፦ የሰላም ውል እና የውስጥ ክፍፍል ሕገ ወጡ ቡድን የሥልጣን ጥመኝነቱን ለማርካት ስፍር ቁጥር የሌላቸው የትግራይ ክልል ተስፋ የሆኑ ወጣቶችን በጦርነት ከማገደ በኋላ የሰላም ስምምነት ተፈረመ። በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ጦርነቱን ለማስቆም የተደረገ ወሳኝ እርምጃ ነበረ። ነገር ግን ከስምምነቱ በኋላ አሁንም ከስህተቱ የማይማረው ይህ ቡድን የተቃርኖ ጉዞውን መቀጠሉን ያረጋገጠበት ጥፋት ፈጸመ። ሕገ ወጡ ቡድን ስምምነቱን በይፋ ከተቀበለው በኋላ ስምምነቱን የሚጥሱ ድርጊቶችን መፈጸም ቀጠለ። መሣሪያ ለማስረከብ ተስማምቶ በስምምነቱ መሠረት መሄድ አቃተው፣ እንቅፋት ፈጠረ። በትጥቅ ውስጥ የቆዩ ወጣቶች ወደ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመለሱ ማድረግ ነበረበት፣ አላደረገም። ይልቅስ ለሌላ ጥፋት ውስጥ ለውስጥ መዘጋጀቱን ተያያዘው። ጊዜያዊ አስተዳደር ለመመስረት ተስማምቶ ወደ ተግባር ከተገባ በኋላ የጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮችን አልቀበልም በማለት ሕገ ወጥነቱን ቀጥሎ ለትግራይ ሕዝብ ሰላም እና እፎይታ የሰጠውን የሰላም ስምምነት አፈረሰ። ከጦርነቱ ማብቃት በኋላ ትኩረት መደረግ የነበረበት የወደሙ አካባቢዎችን መገንባት፣ የተፈናቀሉትን መመለስ እና ሰብዓዊ እርዳታ ማፋጠን ላይ መሆን ሲገባው፣ ሕገ ወጡ ቡድን ወደ ውጭ ይፋ በወጣ የሥልጣን ሽኩቻና የእርስ በእርስ ውንጀላ ውስጥ መዘፈቁ ለሕዝቡ ያለው ግድየለሽነት ማሳያ ሆኖ ተወሰደ። ለጥፋት ተልዕኮው ስኬት በፍጹም የዓላማም ይሁን የትግል አንድነት የለኝም ሲላቸው ከነበሩ የጥፋት ቡድኖች ጋር አበረ። ይህ ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመመሳጠር ሉዓላዊነትን ለማስደፈር እና ሀገር ለማፍረስ በሙሉ አቅሙ መንቀሳቀስ ጀመረ። ልብ ማለት የሚገባን ባህር በርን የሚያክል ጉዳይ እንደ ተራ ሸቀጥ ያየው ቡድን እንዴት ስለ ብሔራዊ ክብር እና ሉዓላዊነት ሊያስብ ይችላል? ሊሆን አይችልም። ተቃርኖ አራት፦ የሕገ ወጡ ቡድን የመጨረሻው የጥፋት ጉዞ ዓለምና የኢትዮጵያ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ሁኔታ በከፍተኛ ሁኔታ ቢቀየርም፣ ሕገ ወጡ ሕወሓት ግን አሁንም በ1960ዎቹ እና 70ዎቹ የትግል ስልት ተከተሏል። ቡድኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከሆኑት ባዕዳን ተልዕኮ ተቀብሎ ከሀገር ውስጥ ባንዳዎች ጋር አብሯል። ‘ጽምዶ’ ከተባለው የጥፋት ስብስብ ፊት አውራሪ በመሆን የለመደውን የተቃርኖ ጉዞ ለመቀጠል ተቅበዝብዟል። የወጣቱን የሥራ፣ የዲሞክራሲ፣ የኢኮኖሚና የዘመናዊነት ጥያቄ በትክክለኛ መንገድ ከመመለስ ይልቅ ወደ ሥልጣን ለመመለስ ለሚያደርገው የቀቢጸ ተስፋ ሙከራ እያደረገ ነው። ከምርጫ ቦርድ ጋር ያለው ሕጋዊ ሰውነት የማጣት አለመግባባት እና በሕጋዊ መንገድ ራሱን ለማደስ ፈቃደኛ አለመሆኑ ቡድኑን በሕግ ፊትም ሆነ በፖለቲካዊ ምህዳሩ ውስጥ ወደ መጨረሻው የመገለልና የውድቀት ምዕራፍ መርቶታል። ዛሬ ግን ትናንት አይደለም። ኢትዮጵያ ዘመኑን በዋጀ አመራር እየተመራች ትገኛለች። ዘመኑን ሙሉ የተቃርኖ ጉዞ ያደረገው ሕገ ወጡ ቡድን ወደ መጨረሻው የፖለቲካ ውድቀት እያመራ ነው። የሕገ ወጡ ቡድን የተቃርኖ ጉዞም የበቃል።
የኢትዮጵያዊያን ምክክር፤ የጋራ ነገን የሚያሻግር የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ድልድይ
Jul 22, 2026 1032
በሚኪያስ ጎቡ መግቢያ፡- ሀገራት ከጦርነት በላይ የሚፈትናቸው ጠላት አለ፤ እርሱም በአንድ ሀገር ልጆች መካከል የሚፈጠረው የመተማመን መሰናክል ነው። መሣሪያ የፈጠረውን ጉዳት እንደገና መገንባት ይቻላል። የተሰበረ ልብና የጠፋ መተማመን ግን በጉልበት አይመለስም። ለዚህም ነው ብዙ ሀገራት ከግጭት በኋላ ወደ ምክክር የሚመለሱት። ብሔራዊ ምክክር የአንድ መንግሥት ፕሮጀክት ወይም የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአንድ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፈው የሰላም ውርስ ነው። የሚጋጩ ሃሳቦች በጠመንጃ ሳይሆን በቃል ሲገናኙ፣ የተለያዩ ትርክቶች በመደማመጥ ሲቀራረቡ፣ ልዩነቶችም የጥላቻ ምንጭ ሳይሆኑ የመግባባት መነሻ ሲሆኑ ነው እውነተኛ ሀገራዊ ምክክር የሚፈጸመው። የዓለም ተሞክሮ እንደሚያሳየው ብሔራዊ ምክክር አንድ ዓይነት ቀመር የለውም። እያንዳንዱ ሀገር በታሪኩ፣ በባህሉ፣ በፖለቲካዊ እውነታውና በማኅበራዊ መዋቅሩ መሰረት የራሱን መንገድ ይመርጣል። ነገር ግን የሁሉም ግብ አንድ ነው፤ ግጭትን በመግባባት፣ ጥላቻን በመተማመን፣ ፍርሃትን በተስፋ መተካት። በአውሮፓ ከኮሙኒዝም ውድቀት በኋላ፣ በአፍሪካ ከአምባገነናዊ አስተዳደሮች ሽግግር ወቅት፣ በደቡብ አሜሪካ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሂደቶችና በዓረቡ ዓለም ከፖለቲካ አብዮቶች በኋላ የተካሄዱ ምክክሮች አንድ ትልቅ ትምህርት ይሰጣሉ። ምክክር ሲታመን ሀገር ያድናል፤ ለፖለቲካ ጥቅም ሲውል ግን ቀውስን ያባብሳል። ይህ የኢትዮጵያም ትልቁ ፈተና ነው። ሀገራዊ ምክክር የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ወገን ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነት ነው። የምንናገረው ቃል፣ የምንጽፈው ሐሳብ፣ የምናዳምጠው አቋምና የምንቀበለው ልዩነት የነገዋን ኢትዮጵያ ይቀርጻሉ። ምክክር የሚጀምረው በአዳራሽ ሳይሆን በሰዎች ልብ ውስጥ ነው፤ የሚሳካውም ከመናገር በላይ በመደማመጥ ሲቻል ነው። ስለዚህ የዛሬው ጥያቄ "ምክክር ይካሄድ ወይ?" የሚል አይደለም። "ምክክሩን ለሀገር የሚበጅ፣ ለትውልድ የሚተርፍ፣ ለታሪክ የሚያስከብር እንዴት እናድርገው?" የሚለው ነው። መልሱም በአካታችነት፣ በእውነት፣ በመከባበርና በሀገርን ከግል ጥቅም በላይ በማስቀደም ውስጥ ይገኛል። ምክክር፤ የሀገር መድኃኒት ወይስ የትውልድ ፈተና? ምክክር ለምን ያስፈልጋል?፡- ማንኛውም ሀገር የሚያድገው በሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ግንባታ ብቻ አይደለም። በሕዝቦቿ መካከል በሚኖረው መተማመን ጭምር እንጂ። መንገድ፣ ድልድይና ፋብሪካ መገንባት ይቻላል፤ ነገር ግን የተሰበረ ማኅበራዊ ትስስር ካልተጠገነ የልማቱ መሠረት ይናወጣል። ስለዚህ ብሔራዊ ምክክር የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን የሀገር የወደፊት ዕጣ ፋንታ የሚወሰንበት የጋራ አስተሳሰብ ሂደት ነው። የምክክሩ ዋና ዓላማ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር አይደለም። ይልቁንም ሁሉም ወገኖች የራሳቸውን እውነት እየገለጹ፣ የሌላውንም እውነት በማዳመጥ የጋራ መግባባት የሚፈጥሩበት ሂደት ነው። እውነተኛ የምክክር ድል የሚለካውም የማን ሃሳብ አሸነፈ ሳይሆን ለሀገር ምን ያህል ሰላምና መተማመን ፈጠረ በሚለው ነው። የዓለም ተሞክሮ የሚያስተምረን፡- የታሪክ ገጾች እንደሚያሳዩት ሀገራት የብሔራዊ ምክክርን መንገድ የመረጡት ሌሎች አማራጮች ሲያቅቷቸው ነው። አንዳንዶቹ የረዥም ጊዜ የፖለቲካ ቀውስ ነበራቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ በዘር፣ በሃይማኖት ወይም በሥልጣን ሽኩቻ ተከፋፍለው ሲራኮቶ የሰነባበቱ ናቸው። ነገር ግን የተሳካላቸው ሀገራት አንድ የጋራ መርህ ነበራቸው፤ የሀገርን ጥቅም ከፓርቲ፣ ከቡድንና ከግል ጥቅም በላይ አስቀድመዋል። ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ ወደ ዴሞክራሲ የተሸጋገረችው በበቀል ሳይሆን በሰለጠነ ምክክር ነው። ፖላንድና ሀንጋሪ የፖለቲካ ሽግግራቸውን በየጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር አሳልፈዋል። ላይቤሪያና ሊባኖስ የጦርነት ቁስላቸውን ለማዳን የመደማመጥን መንገድ መርጠዋል። በተቃራኒው ግን ምክክርን ለፖለቲካ ሕጋዊነት ማግኛ፣ ለሥልጣን ማራዘሚያ ወይም ለውጭ ጫና ማስታገሻ ብቻ ያደረጉ ሀገራት የበለጠ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። ይህም አንድ ግልጽ ትምህርት ይሰጠናል፤ የምክክር ስኬት የሚወሰነው በመድረኩ ሳይሆን በተመካካሪዎች ቅንነት መሆኑን ያስረዳናል። ምክክር የሚጠይቀው ከባድ ኃላፊነት፡- ሀገራዊ ምክክር የኮሚሽን ወይም የመንግሥት ሥራ ብቻ አይደለም። የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነትን የሚጠይቅ የጋራ ነገ አሻጋሪ ድልድይና የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ነው። ፖለቲከኛው የሀገርን ጥቅም ማስቀደም፣ የሚዲያው እውነትን በሚዛናዊነት ማቅረብ፣ የሲቪክ ማኅበራት የተገለሉ ድምፆችን ማሰማት፣ የኃይማኖት ተቋማት ይቅርታና መቻቻልን ማስፋፋት፣ ወጣቱ ከጥላቻ ይልቅ ውይይትን መምረጥና ምሁራን በማስረጃ የተደገፈ ሃሳብ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ማንም ወገን የራሱን አቋም ብቻ ለማስገደድ ከሞከረ፣ ምክክሩ ወደ ክርክር ይቀየራል። ሁሉም ለመረዳት እንጂ ለማሸነፍ ካልመጡ ደግሞ የምክክሩ መንፈስ ይጠፋል። የሀገራዊ ምክክር ትልቁ ድል የሌላውን አቋም መለወጥ ሳይሆን፣ የሌላውን ህመም መረዳት ነው። ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር፤ ልዩነታቸው ምንድን ነው?፡- ብዙ ጊዜ ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር የሚሉት ቃላት በአንድ ትርጉም ይጠቀሳሉ። ነገር ግን በፖለቲካዊና በማኅበራዊ ሂደቶች እያንዳንዳቸው የተለየ ዓላማና ባህሪ አላቸው። ይህንን ልዩነት አለማወቅ ሀገራዊ ምክክርን ከመጀመሪያው ሊያዛባው ይችላል። ውይይት የሐሳብ ልውውጥ ነው። ሰዎች ስለ አንድ ጉዳይ አመለካከታቸውን ይገልጻሉ፣ ይደማመጣሉ። ሁልጊዜ ውሳኔ ላይ ላይደርስ ይችላል። ክርክር የሚያተኩረው የማን ሃሳብ ትክክል እንደሆነ ላይ ነው። የራስን አቋም በማስረጃ ለማስረዳት ይደረጋል፤ አንድ አሸናፊና አንድ ተሸናፊ ሊኖር ይችላል። ድርድር ደግሞ የጥቅም ግጭትን በመካከለኛ መፍትሔ ለመፍታት የሚደረግ ሂደት ነው። እያንዳንዱ ወገን ከአቋሙ በመቀነስ የጋራ መፍትሔ ለማግኘት ይሞክራል። ሀገራዊ ምክክር ግን ከእነዚህ ሁሉ የላቀ ሂደት ነው። ዓላማው ማንንም ማሸነፍ ወይም ማስሸነፍ ሳይሆን የሀገር የወደፊት አቅጣጫ ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር ነው። በምክክር ውስጥ የሚሸነፍ ሰው የለም፤ የሚያሸንፈው ሀገር ነው። የኢትዮጵያ ልዩ እውነታ፡- ኢትዮጵያ ሦስት ሺህ ዘመናትን የተሻገረ በሕብር ያሸበረቀ ታሪክ፣ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ፣ ቋንቋ፣ ባህልና ኃይማኖት ያላት ሀገር ናት። ይህ በሕብር ያሸበረቀ ልዩነት የኢትዮጵያ ጥንካሬ መሆን ሲገባው በተለያዩ ወቅቶች የፖለቲካ አለመግባባቶችና የታሪክ ትርክቶች የመከፋፈል መሣሪያ ሆነው ቆይተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ ዋና ፈተናም ይህ ነው። ሁሉም የራሳቸውን ታሪክ ይዘው ወደ ጠረጴዛው ይመጣሉ፤ ነገር ግን ከጠረጴዛው የሚወጡት አንድ የጋራ የወደፊት ርዕይ ይዘው መሆን አለባቸው። ይህ ቀላል አይደለም። ስለዚህ ምክክሩ ከቃላት በላይ በተግባር የሚገለጥ ቅንነትን ይፈልጋል። የዋናው ምክክር ጉባኤ የህዝብ ወኪል ተመካካሪዎችም ሀገርን የማስቀደም ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ስኬታማ ምክክር የሚመሰረትባቸው አምስት ምሰሶዎች፡- ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ እንዲሆን ቢያንስ አምስት መሠረታዊ ምሰሶዎች ሊኖሩት ይገባል። እነሱም መተማመን፣ አካታችነት፣ እውነት፣ ፍትሕና የጋራ ርዕይ ናቸው። ከሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበራሰብ የሕዝብ ወኪል 4 ሺ ተመካካሪ ኢትዮጵያዊያንም በሀገር ግንባታ ጉዳይ፣ የመንግስት አደረጃጃትና ስርአት ጉዳይ፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬድዋ ከተሞች ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና የመልካም አስተዳዳር ጉዳዮች፣ የሰላም ግንባታ ጉዳዮች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽ ማዕከል እየመከሩ ይገኛል። ሀገራዊ ምክክር ያለፈውን ለመቁጠር ሳይሆን፣ የወደፊቱን ለመገንባት የሚደረግ የጋራ ጉዞ ነው። የኢትዮጵያ መንገድም የልዩነት ግድግዳን የሚያፈርስ የትውልድ አደራና የብሔራዊ መግባባት ማሰሪያ ጥበብና ትልም ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፤ የተገኙ ዕድሎች፣ ዋና ፈተናዎች እና የወደፊት አቅጣጫ በታሪክ ጉዞዋ ውስጥ ኢትዮጵያ ብዙ የፈተና ዘመናትን አልፋለች። አንዳንዶቹ ፈተናዎች ከውጭ ጥቃት የመጡ ቢሆኑም፣ አብዛኞቹ ግን ከውስጣዊ አለመግባባቶች፣ ከተለያዩ የታሪክ ትርክቶች፣ ከፖለቲካ ፉክክርና ከመተማመን እጥረት የተፈጠሩ ናቸው። ስለዚህ የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደት የዛሬን ችግር ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፣ የትውልድ ዕዳን ለማቃለል የተጀመረ ታሪካዊ ሂደት ነው። ይህ ሂደት ቀላል አይደለም። በርካታ ዓመታት የተከማቹ ቅሬታዎች፣ የተለያዩ እውነታዎች፣ የተቃራኒ ትርክቶችና የተለያዩ የፖለቲካ ፍላጎቶች በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መገናኘታቸው በራሱ ትልቅ ፈተና ነው። ነገር ግን ከዚህ በላይ ትልቁ ፈተና ልዩነትን ወደ መግባባት መቀየር ነው። ዕድሎች፤ ሊጠቀሙባቸው የሚገቡ ወሳኝ መስኮቶች፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት ኢትዮጵያ ለብዙ ዓመታት ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ የምታነሳበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። የታሪክ አተረጓጎም፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የሥልጣን ክፍፍል፣ የሀብት አጠቃቀም፣ የፍትሕ ጉዳዮችና የአብሮነት ዕሴቶች በጦርነት ሳይሆን በሐሳብ የሚፈቱበት ዕድል ይፈጥራል። ከዚህም በላይ ምክክሩ የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር የሚያስችል ዕድል ነው። ለብዙ ዓመታት "አሸናፊና ተሸናፊ" በሚለው አስተሳሰብ የተመራውን ፖለቲካ ወደ "አብሮ ማሸነፍ" የሚሸጋግር ከሆነ እውነትም የኢትጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ ጠንካራ መሠረት ያገኛል። በሂደቱ ፊት የሚቆሙ ፈተናዎች፡- ማንኛውም ሀገራዊ ምክክር ከፍተኛ ተስፋ እንደሚፈጥር ሁሉ ከባድ ፈተናዎችንም ይዞ ይመጣል። የመጀመሪያው ፈተና የመተማመን እጥረት ነው። ለብዙ ዓመታት የተገነባ ጥርጣሬ በጥቂት ወራት አይጠፋም። ስለዚህ የምክክሩ ተዓማኒነት በእያንዳንዱ እርምጃ ሊገነባ ይገባል። ሁለተኛው ፈተና የተለያዩ የታሪክ ትርክቶች ናቸው። አንድ ክስተት በአንዱ ወገን የድል ታሪክ ሲሆን፣ በሌላው ወገን የመከራ ታሪክ ሊሆን ይችላል። ይህን ልዩነት በክብር መቀበል እንጂ መግፋት አይቻልም። በሌላ መልኩም የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ ስርጭት ነው። በዲጂታል ዘመን አንድ ያልተረጋገጠ መረጃ በጥቂት ደቂቃዎች ሺዎችን ሊደርስ ይችላል። ስለዚህ የሚዲያ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሚወስዱት ኃላፊነት ከመቼውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። የምሁራንና የመገናኛ ብዙኅን ሚና፡- በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ምሁራን ስሜትን ሳይሆን ማስረጃን ማቅረብ አለባቸው። የማኅበረሰብ ችግሮችን በሳይንሳዊ ጥናት መተንተን፣ ከሌሎች ሀገራት ልምድ መማርና አማራጭ መፍትሔዎችን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። መገናኛ ብዙኅንም በዚህ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና አላቸው። መገናኛ ብዙኅን ወሬን ከማባዛት ይልቅ እውነትን ማጣራት፣ ልዩነትን ከማባባስ ይልቅ መግባባትን ማጎልበት፣ ስሜትን ከማቀጣጠል ይልቅ እውነታን ማቅረብ አለበት። ምክክሩን የሚያጠናክር የመገናኛ አውታር ታሪክ ይሠራል፤ የሚያደናቅፍ ደግሞ በታሪክ ይጠየቃል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ቀን የሚጠናቀቅ ክስተት አይደለም። ምክክር በትውልድ የሚገነባ የፖለቲካ ባህል ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራውን ሊጨርስ ይችላል፤ ነገር ግን የመደማመጥ ባህል በሕዝብ ውስጥ ካልሰረጸ የምክክሩ እውነተኛ ዓላማ አይሳካም። የዛሬ ውሳኔ፤ የነገ ኢትዮጵያ፡- አንዳንድ የታሪክ ወቅቶች በየቀኑ አይመጡም። አንዳንድ ውሳኔዎችም የአንድ መንግሥት ዘመንን ብቻ ሳይሆን የትውልዶችን ዕጣ ፈንታ ይወስናሉ። ሀገራዊ ምክክር የእነዚህ ታሪካዊ ውሳኔዎች አንዱ ነው። ዛሬ በምንመርጠው የምክክር ባህል፣ በምንገነባው መተማመንና በምናሳየው የፖለቲካ ብስለት ላይ የነገዋን የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ተምሳሌት ኢትዮጵያ ያንፃል። ምክክር ሁሉንም ችግር በአንድ ጊዜ የሚፈታ አስማታዊ መፍትሔ አይደለም። ነገር ግን ጦርነትን ከውይይት፣ ጥላቻን ከመቻቻል፣ መከፋፈልን ከመተባበር የሚተካ ብልህ መንገድ ነው። የሚያደርገውም ልዩነቶችን ማጥፋት ሳይሆን ልዩነቶችን በአንድ ሀገር ጣሪያ ስር እንዴት እንደሚኖሩ የጋራ ሕግና ሥርዓት መፍጠር ነው። በእርግጥ ኢትዮጵያ ከባድ ፈተናዎችን አሳልፋለች። የፖለቲካ አለመተማመን፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የፀጥታ ችግሮች፣ የኢኮኖሚ ጫናዎችና የማኅበራዊ ስብራቶች በቀላሉ የሚያልፉ አይደሉም። ይሁን እንጂ እነዚህን ችግሮች በጥይት ከመፍታት ይልቅ በምክክር ለመፍታት መሞከር በራሱ የታሪክ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ ግን የአንድ ተቋም ብቻ አይደለም። የመንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኅን ተቋማት፣ የምሁራን፣ የወጣቶች፣ የሴቶችና የእያንዳንዱ ዜጋ የጋራ ኃላፊነት ነው። የሀገር ዕጣ ፋንታ ለአንድ ቡድን ብቻ የሚተው አይደለም፤ በጋራ የሚገነባ እንጂ። ከምክክር ወደ ባህል፡- ምክክሩ ተጠናቀቀ ማለት የሀገሪቱ ችግሮች ተፈቱ ማለት አይደለም። እውነተኛው ስኬት የሚለካው የመደማመጥ ባህል በማኅበረሰቡ ውስጥ ሲሰርጽ ነው። በትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በመገናኛ ብዙኅን፣ በፖለቲካ ተቋማትና በየቤቱ የመነጋገር ባህል ካልጠነከረ፣ ምክክሩ የሰነድ ውጤት ብቻ ሆኖ ይቀራል። የእውነተኛ ዴሞክራሲ መሠረት ተመሳሳይ አስተሳሰብ መኖር አይደለም፤ የተለያዩ አስተሳሰቦችን በሰላም የመቀበል ባህል መኖር ነው። ልዩነት የችግር ምንጭ ሳይሆን የጥንካሬ ምንጭ ሲሆን ነው አንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም የምታገኘው። የማጠቃለያ፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት የሚያስፈልገው ብልህ አመራር ብቻ አይደለም፤ ታጋሽ ዜጎችንም ይፈልጋል። ሀገር የምትገነባው በግንብ ሳይሆን በመተማመን ነው። ሰላም የሚጸናውም በፍርሃት ሳይሆን በፍትሕ ነው። ዛሬ የምንመርጠው የምክክር መንገድ ነገ ለልጆቻችን የምንተወው ታሪክ ይሆናል። ስለዚህ በኢትዮጵያን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተደራጅተው የሚመከርባቸው ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የዛሬ አጀንዳ ብቻ አይደሉም፤ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚቀርጽ የትውልድ አደራ እንጂ። የዋናው ምክክር ጉባኤ ተመካካሪ የሕዝብ ወኪሎችም ከግልና ቡድን ፍላጎት ይልቅ የቀጣዩን ትውልድና ሀገርን ማስቀደም ይጠበቅባቸውል። ምክክር የቃላት ልውውጥ ብቻ አይደለም፤ የተሰበረ መተማመንን የሚጠግን፣ የተከፋፈለ ማኅበረሰብን የሚያቀራርብ፣ የትውልድ ታሪክን በአዲስ ተስፋ የሚጽፍ ሀገራዊ ጥበብ ነው። የምንወስነው ዛሬ የምንወርሰውን ነገ ይበይናል። ምክክር የሀገር መድኅን ነው፤ ኢትዮጵያም እየመከረች ነው።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 11589
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 21443
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14468
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20220
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
በምክክር እንጂ በመሳሪያ ድምጽ ሀገር አይገነባም
Aug 8, 2026 252
ኢትዮጵያ የዛሬ ማንነቷና ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እዚህ እንድትደርስ በርካታ ውጣውረዶችን አልፋለች። በቀደመ ታሪኳም ዜጎች በራሳቸው የውስጥ ጉዳይ መስማማት ባለመቻል እርስ በእርስ ካደረጓቸው ግጭቶች ባለፈ የውጭ ሃይሎችም የራሳቸውን አሉታዊ ጫና ሲፈጥሩ ቆይተዋል፤ አሁንም ይህንኑ ለማስቀጠል ተላላኪዎቻቸውን ለመጠቀም ሲሞክሩ ይታያል። በአንድ ሃገር ውስጥ የማያግባቡ ጉዳዮች በየትኛውም አጋጣሚና የታሪክ ምዕራፍ ሊያጋጥሙ ይችላሉ። እነዚህን ችግሮች በሃይል ለመፍታት የሚደረገው የመሳሪያ ትንቅንቅ ግን አክሳሪና ዘመን እያለፈበትም ነው። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ሰላማዊ የእድገት ጉዞ ለማወክ የህዝቦቿን አንድነት ለመበጥበጥ ከቅርብም ሆነ ከሩቅ የሚመጡ ጠላቶች ጠፍተው አያውቁም። በየዘመናቱ የተሻገርናቸው የታሪክ ስብራቶችን ፣ የመብት ጥያቄዎችንና ሌሎችንም መነሻ በማድረግ በውስጥ ባንዳዎች እና በውጭ ባዳዎች አማካኝነት የማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ለመክተት፣ የብልጽግና ጉዞዋን ለማደናቀፍ የሚደረጉ ሴራዎች ዛሬም ላይ ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት ተሰሚነትና ተጽዕኖ የሚያሳምማቸው ለዜጎቿን እኩል ተጠቃሚነትና ብልጽግና መረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚያስጨንቃቸው እነዚህ ሃይሎች በመብት ፣ በነጻነት፣ በዴሞክራሲ፣ በማንነትና በሌሎችም የሃሰት ትርክቶች መነሻነት በሩቅ ቢያቅታቸው በቅርብ የውስጥ ተላላኪ ባንዳዎችን እያደራጁ በጀት መድበው የጦር መሳሪያ አቅርበው ሀገር የማፍረስ ሙከራቸውን አላቋረጡም። በመደመር እሳቤ ሁሉንም በአንድ ላይ በማቀራረብና የጋራ ትርክቶችን በመገንባት ከልዩነት ይልቅ የሚያቀራርቡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ዘላቂ ልማቷን መፃኢ ብሩህ ተስፋዋን ለማለምለም በሁሉም ዘርፍ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ተሳትፎ እየሰራች መሆኗም ምቾት ነስቷቸዋል። በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሔደ ያለውና ወርቃማው እድል ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ፣ የሚያስችሉ ወሳኝ ምዕራፎች ላይ ደርሷል ። በዚህ የምክክር ሒደት በሀገሪቱ የትኛውም ጥግ ያለ ዜጋ እንዲሁም በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የተወከሉበት ፣ የብሔር፣ የፖለቲካ አመለካከትና የሃይማኖት ልዩነት የማያደናቅፉት ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እየተካሔደ ይገኛል። ጥያቄያችንን በጠብመንጃ አፈሙዝ እንፈታለን ያሉ ታጣቂዎችም ብረት በማስቀመጥ አጀንዳዎቻቸውን ይዘው ወደ ጠረጴዛው ቀርበዋል። ልክ ናቸው ሀገር ከሁሉም ነገር ትበልጣለችና ይሄንን ወርቃማ እድል ለመጠቀም ማሰብ ትክክለኛው ውሳኔ ነው። በትጥቅ ትግል ጥያቄያችንን እንመልሳለን በሚል ሽፋን የሌሎችን አጀንዳ ለማሳካት የሚደረግ ጥረት የሃገርና የትውልድ ጠባሳ ከማስቀመጥና የታሪክ ተወቃሽ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው መገንዘብ ብልህነት ነው። የዚህ ምክክር ተሳታፊ/ተመካካሪ ከሆኑት የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) አመራር ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በዚህ ይስማማሉ ። ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ተስፋ የጣልንበት፣ በንግግር፣ በምክክር ሀገራችንን የምናስቀጥልበት፣ ሁሉም ተነጋግሮ ተመካክሮ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ከችግሮች ነፃ የሚያደርግበት ነው ይላሉ። ምክክሩ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚነጋገርበት፣ የሚመካከርበት እና በሃሳብ የበላይነት ጠንካራ ሃገር የሚፈጠርበት መልካም የታሪክ አጋጣሚ መሆኑንም ይናገራሉ። በምክክር፣ በድርድር የሕዝብን ጥያቄ በመመለስ ሀገርን የምናስቀጥልበትና የውጭ ኃይሎችን ጣልቃ ገብነት የምናስወግድበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ነው ብለዋል። የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራር የቀድሞ ታጣቂ ጃል ሰኚም ይሄንኑ ሃሳብ ይጋራሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ለዓመታት የቆዩ ልዩነቶችን ለመፍታት ሀገራዊ ምክክር መዘጋጀቱ ትልቅ እርምጃ እንደመሆኑ እሳቸውም ያላቸውን ሀሳብ በማንጸባረቅ እየመከሩ ይገኛሉ። እርሳቸውና ቡድናቸው ከዚህ ቀደም የትጥቅ ትግልን በመምረጥ ጫካ ገብተው እንደነበር አስታውሰው፤ ችግሮችን በመሳሪያ ከመፍታት ይልቅ በሰላማዊ የምክክር መድረክ መፍታት ጥሩ አማራጭ መሆኑን አምነው ወደ ሰላም መንገድ መምጣታቸውንም ተናግረዋል። ችግሮቻቸውን በምክክር የፈቱ ሀገራት በሁሉም ዘርፍ ዕድገታቸውን የሚያስቀጥሉ ሲሆኑ ወደ ትጥቅ ትግል ያመሩና ግጭት ውስጥ የገቡት ደግሞ በፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውድቀት ለከፋ ድህነት መዳረጋቸውን ጠቅሰዋል። የጦር መሣሪያ በመነቅነቅና ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ በመግባት የሚፈታ ችግር እንደሌለ የሚናገሩት ደግሞ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ(አብን) አመራሩ ተመካካሪ ጣሒር መሀመድ ናቸው። ጫካ ባለውና እዚህ ባለው ሰው መካከል ምንም ዐይነት የዜግነት ልዩነት እንደሌለ ገልጸው ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሃሳብ ለመታገል ልዩነቱን ለማቅረብ የፈለገ ሁሉም ዜጋ በምክክሩ የመሳተፍ ነጻነት እንዳለው ገልጸዋል። በሃገራዊ ምክክሩ ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሰላማዊ መድረክ መወያየት የተመረጠበት ዋና ምክንያት ዘላቂ ሰላም፣ አገራዊ መግባባት እና የፖለቲካ ባህል ለውጥ ለማምጣት ነው:: የትጥቅ ትግል የዜጎችን ህይወት ያጠፋል፣ መሰረተ ልማቶችን ያወድማል፤ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድቀትንም ያመጣል: ፤ ሰላማዊ መድረክ ግን ያለምንም ደም መፋሰስ ሃሳብን በሃሳብ ለመሞገት እድል ይሰጣል:: በኃይል የሚመጣ ለውጥ ብዙውን ጊዜ አሸናፊና ተሸናፊን ስለሚፈጥር የቁስል እና የቂም ዑደትን ያስቀጥላል:: በሰላማዊ ውይይት የሚገኝ መፍትሄ ግን የሁሉንም ወገን ስጋት እና ፍላጎት ያገናዘበ በመሆኑ ዘላቂነት ይኖረዋል:: ሃገራዊ ምክክሩ የታጠቁ አካላትም ጭምር መሳሪያቸውን አስቀምጠው በሃሳብ እንዲፎካከሩ መንገድ ከፍቷል። ይህ ታሪካዊና ወርቃማ እድል ኢትዮጵያዊንን አግባብቶ ወደተረጋጋችና የበለጸገች ሃገር የሚመራ በመሆኑ ስኬታማነቱ አያጠራጥርም። ለእድለኛው ትውልድ ያጋጠመው ወርቃማው ስጦታ ሃገራዊ ምክክር የተቋቋመለትን ዓላማ ያሳካል።
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 1166
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።