አርእስተ ዜና
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አመራሮች እና ከፍተኛ ሰልጣኝ መኮንኖች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝት አደረጉ
May 30, 2023 34
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) ፦የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አመራሮች እና ከፍተኛ ሰልጣኝ መኮንኖች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝት አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን መልዕክት የጽህፈት ቤታቸው ኃላፊ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ያቀረቡ ሲሆን፤ የአገር መከላከያ ሰራዊት በሁሉም አውዶች የአገርን ደህንነት እና ሉዓላዊነት ከጥቃት ለመጠበቅ ከሕዝብ አብራክ ወጥቶ ለሕዝብ እየኖረ ያለ የዜጎች አለኝታ በመሆኑ ላቅ ያለ ክብር የሚገባው ነው ብለዋል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና መከላከያ ሰራዊት የአገር እና የሕዝብ መከታ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ቡልቲ ታደሰ በበኩላቸው ኮሌጁ በሰው ኃይል ግንባታ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማር እና ስልጠናዎችን በመስጠት በሰው ኃይል ግንባታ ብቁ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ሰራዊቱ በዓለም ሰላም ማስከበር እና በሌሎች ተልኮዎች ውጤታማነቱን ማስመስከሩን ገልጸው ኮሌጁ በቀጣይም ስራውን በተሻለ ተግባር እንዲከውን የሚያስችል ስልጠና እየሰጠ ነው ብለዋል ። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት የፖለቲካ ሳይንስ መሪ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ዳር እስከዳር ታዬ “የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊስ ትናንት እና ዛሬ” በሚል የመወያያ ጽሑፍ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል። በውይይቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መሰጠቱን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በመዲናዋ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትና የአገልግሎት መቆራረጥ ችግርን ለመቀነስ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ነው- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
May 30, 2023 28
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና የአገልግሎት መቆራረጥ ችግርን ለመቀነስ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። በአዲስ አበባ ከተማ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና አገልግሎት መቆራረጥ ችግርን ለመቅረፍ የፌዴራል እና የከተማ አስተዳድሩ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች በተገኙበት ውይይት ተካሄዷል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ አዲስ አበባ የዲፕሎማሲ ማዕከል እና ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ፍሰት ያለባት ከተማ በመሆኗ፤ ደረጃዋን የሚመጥን የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል። በሰው ሰራሽና በተፈጥሯዊ ምክንያቶች በመሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርስን ጉዳት በኃይል አቅርቦት ላይ መቆራረጥ እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል። የኃይል መቆራረጥ በንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ላይም ጫና እያሳደረ መሆኑን ገልጸው፤ ከተማ አስተዳድሩ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማስፋፋት የሚያስችሉ መሰረተ ልማቶችን እያስፋፋ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ በበኩላቸው አዲስ አበባን ጨምሮ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማሻሻል አስቻይ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በአዲስ አበባ ከመሰረተ ልማት እድገቷ ጋር ተያይዞ የኤሌክትሪክ ፍላጎትን ለማሳደግና ለማዘመን ከፍተኛ በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። ለአብነትም ከሰው ንክኪ ነጻ ቆጣሪዎችን ለኢንዱስትሪ ደንበኞች መቅረቡን እና ደንበኞች ቅሬታቸውን በቴክኖሎጂ ተጠቅመው በማኅበራዊ ሚዲያ የሚያቀርቡበት ስርዓት መዘጋቱን አንስተዋል። በሌላ በኩል የአገልግሎት ለማሳለጥና ከከተማ አስተዳድሩ ጋር በቅርበት ለመስራት ያልተማከለ አደረጃጀት መፍጠሩንም ነው አቶ ሽፈራው ያስረዱት። የኃይል መቆራረጥ ችግር ከመቅረፍ ባሻገር የኃይል አቅርቦት እና አገልግሎት ተደራሽ ባልሆነባችው የመዲናዋ አካባቢዎች አገልግሎቱን ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በምክክር መድረኩ ላይ የዘርፉን ችግሩን ለማቃለል የሚያስችል የ90 ቀናት እቅድ የሚያወጣ ቡድን ተቋቁሟል።
ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና በሰዎች የመነገድ ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የባለድርሻ አካላት የትብብር ጥምረት ሊጠናከር እንደሚገባ ተጠቆመ
May 30, 2023 24
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ)፡- ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና በሰዎች የመነገድ ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የባለድርሻ አካላት የትብብር ጥምረት ሊጠናከር እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን በሚመለከት በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ ተግባራትን ማስፋት የሚያስችል አገር አቀፍ የልምድ ልውውጥ መድረክ ተካሂዷል። የልምድ ልውውጥ መድረኩ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና በአማራ ክልል መካከል የተከናወነ ሲሆን፤ በቀጣይም ወደ ሌሎች ክልሎች እንደሚሰፋም ተጠቁሟል፡፡   በመረሓ-ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የስራ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፣ የከተማዋ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተክሌ በዛብህ እና የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ገረመው ገብረፃዲቅ ተገኝተዋል። በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የምክር ቤት አባላት እንዲሁም የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ታድመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የስራ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፤ በኢትዮጵያ ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር፣ በሰዎች የመነገድና በህገ ወጥ መንገድ ለውጭ አገራት የስራ ስምሪት ዜጎችን የመላክ ተግባር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ በዚህም መንግስት የችግሩን አሳሳቢነት በመገንዘብ ዘርፈ ብዙ የመከላከልና የመቆጣጠር ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ነው ያሉት። ይህንን ተግባር በማጠናከር ረገድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘርፉ ከሚሰሩ አጋር አካላት ጋር የትብብር ጥምረት ማቋቋሙን አንስተዋል። ጥምረቱ በከተማዋ ፍትህ ቢሮ፣በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የተዋቀሩበት መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡ ጥምረቱ የሰዎች ዝውውር በስፋት የሚፈፀሙባቸው አካባቢዎችን በመለየት የቁጥጥርና የክትትል ስራዎች ማከናወን ዋነኛ ተግባሩ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በተጨማሪም በጉዳዩ ላይ የማህበረሰቡን ግንዛቤ ማስፋትና ተጠያቂነትን ማስፈን ላይ እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡ በመሆኑም ይህንን የትብብር ጥምረት በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች በማስፋት ወንጀሉን ማስቆምና የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል። የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ተክሌ በዛብህ በበኩላቸው ከተማዋ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀል በሰፋት ከሚፈጸምባቸው አካባቢዎች መካከል አንዷ መሆኗን አንስተዋል፡፡ ወንጀሉ በህጻናትና በሴቶች ላይ ጎልቶ እየተፈጸመ መሆኑ ደግሞ ችግሩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ በሰዎች የመነገድ፣ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ የማሻገርና ህገ-ወጥ የስራ ስምሪትን በሚመለከት ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በመፈረም ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝም ጨምረው ገልጸዋል። የወንጀሉን አስከፊነትና በዜጎች ላይ የሚያደርሰውን አሉታዊ ተጽእኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት ተጠያቂነትን የማስፈን ስራ እየተከናወነ ስለመሆኑም አንስተዋል። ይሁን አንጂ እነዚህ ወንጀሎች አይነታቸውና ሁኔታቸው እየተቀያየረ የሚፈጸሙ በመሆናቸው የመከላከል ስራውን በተሻለ ቅንጅት ማከናወን ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በመሆኑም የተቋቋመውና በስራ ላይ ያለውን የትብብር ጥምረት አቅም ማሳደግና ወደ ሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች የማስፋትና የልምድ ልውውጥ የማድረግ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ገረመው ገብረጻዲቅ እንዲሁ በክልሉ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀል በስፋት እንደሚፈጸም ተናግረዋል፡፡ በዚህም ህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎችንና አካባቢዎችን በመለየትና ልዩ ክትትል በማድረግ ወንጀሉን የመከላከልና ተጠያቂነትን የማስፈን ስራው በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑም አብራርተዋል። ይሁን እንጂ ወንጀሉ የሚፈጸምበት ሁኔታ በእጅጉ ውስብስብ በመሆኑ የአጋር አካላት ድጋፍና እገዛ ያስፈልጋል ብለዋል። በመሆኑም ዛሬ በተደረገው የልምድ ልውውጥ የትብብር ጥምረትን ማቋቋም ያለው ጠቀሜታ የጎላ በመሆኑ ተግባሩን ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።  
ከሀገር ውስጥ የስኳር ምርት በተጨማሪ 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት ዝግጅት ተደርጓል- የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር
May 30, 2023 21
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015(ኢዜአ)፡- ከሀገር ውስጥ የስኳር ምርት በተጨማሪ 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት መንግስት በዝግጅት ላይ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የበጀት ምንጫቸውን ለብሔራዊ ባንክ አሳውቀው በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን ከውጭ እንዲያስገቡ ከተፈቀድላቸው ባለኃብቶች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ የዘይት፣ ስኳር እና ሌሎችም መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች እጥረትና የዋጋ ንረት ለመቆጣጠር መንግስት ለሀገር ውስጥ ባለኃብቶች ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ ይታወቃል፡፡ በዚህም ባለፉት አስር ወራት 411 አስመጭዎች በፍራንኮ ቫሉታ የተሳተፉ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የዘይት አቅርቦት 85 በመቶ መሸፈን ተችሏል፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በልሁ፤ መንግስት የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ፍራንኮ ቫሉታ በመፍቀድና በመሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች በታክስ መልክ ያገኘው የነበረውን 10 ቢሊየን ብር አጥቷል፡፡ በፍራንኮ ቫሉታ የሚሳተፉ አስመጭዎችን አገልግሎት ከማሳለጥ ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶች በበቂ ሁኔታ እንዲቀርቡ ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥሯል ብለዋል፡፡ በመሆኑም መንግስት ለአምስት የአገር ውስጥ የተጣራ ዘይት አምራች ድርጅቶች የማምረት አቅማቸውን ታሳቢ በማድረግ 50 ሚሊየን ዶላር እንደመደበላቸው ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል በሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች 650 ኩንታል ስኳር ተመርቶ ለገበያ እየቀረበ መሆኑን ጠቅሰው፤ በስኳር ኮርፖሬሽን በኩል ተጨማሪ 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ለአብነት በፍራንኮ ቫሉታ በአማካኝ በ342 ብር ወደ አገር ወስጥ የሚገባ ባለ አምስት ሊትር ዘይት የተለያዩ የግብይት ሰንሰለቶችን አልፎ ለሸማቹ እስከ 1 ሺህ ብር በሚደርስ የተጋጋነ ዋጋ እየቀረበ መሆኑ ተገልጿል። በመሆኑም በፍራንኮ ቫሉታ ምርታቸውን ወደ ሀገር ውስጥ ለሚያስገቡት አስመጭዎች ቀጥታ ከሸማቹ ጋር እንዲገናኙ የቅዳሜና እሁድ ገበያን ማስፋት እንደ አማራጭ ተይዟል ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባና በክልሎች እስከ 1 ሺህ ነጋዴዎችና ሸማቾች በቀጥታ የሚገናኙበት የቅዳሜና እሁድ የገበያ ሰንሰለት ለመፍጠር መልካም ጅምር ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና የዋጋ ንረትን ለመግታት አቅርቦትና ፍላጎቱን የማመጣጠንና ስርጭቱን ፍትሃዊ የማድረግ ስራ በስፋት ይከናወናል በማለት ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከብሔራዊ ባንክ ዶላር የሚያገኙ ድርጅቶች ከስምንት በመቶ በላይ ትርፍ እንዳያሰሉ መደረጉን ለአብነት ጠቅሰዋል። በፍራንኮ ቫሉታም ሆነ በማንኛውም መንገድ ከውጭ ያስገቡትን ምርት መጋዘን ውስጥ ማከማቸት በህግ ያስጠይቃል፤ መንግስትም ተከታትሎ እርምጃ ይወስዳል ሲሉ አረጋግጠዋል።      
በመዲናዋ በተለያዩ አካባቢዎች ህዝብን እያማረሩ ያሉ ህገ-ወጥ ጫኝና አውራጆች ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወስዷል- የአዲስ አበባ ሰላምና  ጸጥታ አስተዳደር  ቢሮ
May 30, 2023 47
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ህዝብን እያማረሩ ያሉ ህገ-ወጥ ጫኝና አውራጆች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ፤ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች በኢ-መደበኛ መንገድ የተደራጁ ጫኝና አውራጆች ከመጠን በላይ በማስከፈል እና ለህግና ስርዓት ተገዥ ባለመሆን ህዝብን እያማረሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ችግሩ በስፋት እንደሚስተዋል ገልጸው፤ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የ44 ማህበራት አባል የሆኑ 505 ጫኝና አውራጆች በህግ እንዲጠየቁ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በተገልጋይ ላይ ድብደባና ሌሎችም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ 97 ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡ በቀጣይም የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኃላፊዋ አረጋግጠዋል፡፡    
የሚታይ
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አመራሮች እና ከፍተኛ ሰልጣኝ መኮንኖች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝት አደረጉ
May 30, 2023 34
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) ፦የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አመራሮች እና ከፍተኛ ሰልጣኝ መኮንኖች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝት አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን መልዕክት የጽህፈት ቤታቸው ኃላፊ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ያቀረቡ ሲሆን፤ የአገር መከላከያ ሰራዊት በሁሉም አውዶች የአገርን ደህንነት እና ሉዓላዊነት ከጥቃት ለመጠበቅ ከሕዝብ አብራክ ወጥቶ ለሕዝብ እየኖረ ያለ የዜጎች አለኝታ በመሆኑ ላቅ ያለ ክብር የሚገባው ነው ብለዋል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና መከላከያ ሰራዊት የአገር እና የሕዝብ መከታ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ቡልቲ ታደሰ በበኩላቸው ኮሌጁ በሰው ኃይል ግንባታ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማር እና ስልጠናዎችን በመስጠት በሰው ኃይል ግንባታ ብቁ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ሰራዊቱ በዓለም ሰላም ማስከበር እና በሌሎች ተልኮዎች ውጤታማነቱን ማስመስከሩን ገልጸው ኮሌጁ በቀጣይም ስራውን በተሻለ ተግባር እንዲከውን የሚያስችል ስልጠና እየሰጠ ነው ብለዋል ። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት የፖለቲካ ሳይንስ መሪ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ዳር እስከዳር ታዬ “የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊስ ትናንት እና ዛሬ” በሚል የመወያያ ጽሑፍ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል። በውይይቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መሰጠቱን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሀገር ውስጥ የስኳር ምርት በተጨማሪ 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት ዝግጅት ተደርጓል- የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር
May 30, 2023 21
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015(ኢዜአ)፡- ከሀገር ውስጥ የስኳር ምርት በተጨማሪ 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት መንግስት በዝግጅት ላይ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የበጀት ምንጫቸውን ለብሔራዊ ባንክ አሳውቀው በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን ከውጭ እንዲያስገቡ ከተፈቀድላቸው ባለኃብቶች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ የዘይት፣ ስኳር እና ሌሎችም መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች እጥረትና የዋጋ ንረት ለመቆጣጠር መንግስት ለሀገር ውስጥ ባለኃብቶች ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ ይታወቃል፡፡ በዚህም ባለፉት አስር ወራት 411 አስመጭዎች በፍራንኮ ቫሉታ የተሳተፉ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የዘይት አቅርቦት 85 በመቶ መሸፈን ተችሏል፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በልሁ፤ መንግስት የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ፍራንኮ ቫሉታ በመፍቀድና በመሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች በታክስ መልክ ያገኘው የነበረውን 10 ቢሊየን ብር አጥቷል፡፡ በፍራንኮ ቫሉታ የሚሳተፉ አስመጭዎችን አገልግሎት ከማሳለጥ ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶች በበቂ ሁኔታ እንዲቀርቡ ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥሯል ብለዋል፡፡ በመሆኑም መንግስት ለአምስት የአገር ውስጥ የተጣራ ዘይት አምራች ድርጅቶች የማምረት አቅማቸውን ታሳቢ በማድረግ 50 ሚሊየን ዶላር እንደመደበላቸው ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል በሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች 650 ኩንታል ስኳር ተመርቶ ለገበያ እየቀረበ መሆኑን ጠቅሰው፤ በስኳር ኮርፖሬሽን በኩል ተጨማሪ 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ለአብነት በፍራንኮ ቫሉታ በአማካኝ በ342 ብር ወደ አገር ወስጥ የሚገባ ባለ አምስት ሊትር ዘይት የተለያዩ የግብይት ሰንሰለቶችን አልፎ ለሸማቹ እስከ 1 ሺህ ብር በሚደርስ የተጋጋነ ዋጋ እየቀረበ መሆኑ ተገልጿል። በመሆኑም በፍራንኮ ቫሉታ ምርታቸውን ወደ ሀገር ውስጥ ለሚያስገቡት አስመጭዎች ቀጥታ ከሸማቹ ጋር እንዲገናኙ የቅዳሜና እሁድ ገበያን ማስፋት እንደ አማራጭ ተይዟል ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባና በክልሎች እስከ 1 ሺህ ነጋዴዎችና ሸማቾች በቀጥታ የሚገናኙበት የቅዳሜና እሁድ የገበያ ሰንሰለት ለመፍጠር መልካም ጅምር ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና የዋጋ ንረትን ለመግታት አቅርቦትና ፍላጎቱን የማመጣጠንና ስርጭቱን ፍትሃዊ የማድረግ ስራ በስፋት ይከናወናል በማለት ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከብሔራዊ ባንክ ዶላር የሚያገኙ ድርጅቶች ከስምንት በመቶ በላይ ትርፍ እንዳያሰሉ መደረጉን ለአብነት ጠቅሰዋል። በፍራንኮ ቫሉታም ሆነ በማንኛውም መንገድ ከውጭ ያስገቡትን ምርት መጋዘን ውስጥ ማከማቸት በህግ ያስጠይቃል፤ መንግስትም ተከታትሎ እርምጃ ይወስዳል ሲሉ አረጋግጠዋል።      
በመዲናዋ በተለያዩ አካባቢዎች ህዝብን እያማረሩ ያሉ ህገ-ወጥ ጫኝና አውራጆች ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወስዷል- የአዲስ አበባ ሰላምና  ጸጥታ አስተዳደር  ቢሮ
May 30, 2023 47
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ህዝብን እያማረሩ ያሉ ህገ-ወጥ ጫኝና አውራጆች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ፤ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች በኢ-መደበኛ መንገድ የተደራጁ ጫኝና አውራጆች ከመጠን በላይ በማስከፈል እና ለህግና ስርዓት ተገዥ ባለመሆን ህዝብን እያማረሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ችግሩ በስፋት እንደሚስተዋል ገልጸው፤ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የ44 ማህበራት አባል የሆኑ 505 ጫኝና አውራጆች በህግ እንዲጠየቁ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በተገልጋይ ላይ ድብደባና ሌሎችም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ 97 ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡ በቀጣይም የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኃላፊዋ አረጋግጠዋል፡፡    
በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ማህበራዊ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ጃፓን እንደምትደግፍ አምባሳደር ኢቶ ታካኮ ገለጹ
May 30, 2023 25
ዲላ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ማህበራዊ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የጃፓን መንግስት እንደሚደግፍ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ ገለጹ። በጌዴኦና ምዕራብ ጉጂ ዞኖች አጎራባች አካባቢዎች ማህበራዊ ልማትና መስተጋብርን የሚያጎለብት ፕሮጀክት ዛሬ በዲላ ከተማ ይፋ ሆኗል። ፕሮጀክቱ ከጃፓን መንግስት በተገኝ 83 ሚሊዮን ብር ድጋፍ በቀጣይ ሦስት ዓመታት በዞኖቹ ባሉ አራት አጎራባች ወረዳዎች የሚተገበር መሆኑም ተመላክቷል። በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ ፕሮጀክቱ ይፋ ሲደረግ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ማህበራዊ ልማትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማገዝ የጃፓን መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል።   በተለይ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም መሰረት ይጥላል ተብሎ ለሚጠበቀው ለኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን የ3 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ መደረጉንም ለአብነት አንስተዋል። ዛሬ በሁለቱ ዞኖች አጎራባች አካባቢዎች ይፋ የተደረገው ፕሮጀክት የዚህ ድጋፍ አካል መሆኑን ጠቅሰው፣ "ፕሮጀክቱ ለሰላም ግንባታ፣ ለማህበራዊ ኑሮ መሻሻልና ለማህበራዊ ትስስር ጠቀሜታው የጎላ ነው" ብለዋል። በተለይ አጎራባች አካባቢዎችን በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላም ከማስፈን ባለፈ ሴቶችና ወጣቶች ኑሯቸውን ሊያሻሽሉ በሚችሉ ስራዎች እንዲሳተፉ የፋይናንስ ድጋፍ እንደሚደረግ አመላክተዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላምና ማህበራዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በጃፓን መንግስት በኩል መሰል ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በሁሉቱ ዞኖች አጎራባች አካባቢዎች ከዚህ ቀደም የነበረው የጸጥታ ችግር ሙሉ በሙሉ ተፈትቶ ህብረተሰቡ ፊቱን ወደልማት ማዞሩን ያነሱት ደግሞ በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ ጉጂ ዞን የፀጥታ አስተዳደር የግጭት ፈጥኖ ምላሽ አስተባባሪ አቶ አየለ ወላሳ ናቸው። በዞኑ ገላናና ቡሌ ሆራ ወረዳዎች በተደጋጋሚ የሚከሰተውን የድርቅና የጎርፍ አደጋ ችግሮች ለማቃለል የማህበረሰብ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም መጀመሩ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፕሮጀክቱ በአካባቢው የልማትና የማህበራዊ መስተጋብርን በሚያጎለብት መልኩ ተፈጻሚ እንዲሆን በዞኑ በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግም ተናግረዋል። በደቡብ ክልል የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ክትትል አስተባባሪ አቶ ከፍያለው ቢሬ በበኩላቸው፣ ሁለቱን ዞኖች በመሰረተ ልማትና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነታቸውን በማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው ፕሮጀክት ይህንን ከማጠናከር ባለፈ ህብረተሰቡ ሰርቶ እንዲለወጥ የፋይናንስ ድጋፍና ስልጠና በመስጠት የማህበረሰቡን ኑሮ ለማሻሻል አስተዋጾው የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመድረኩ የጃፓን ኤምባሲና የሁለቱ ዞኖች የሥራ ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ፕሮጀክቱ ከ40 ሺህ በላይ አባወራና እማወራዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ተገልጿል።  
ማስታወቂያ
ፖለቲካ
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አመራሮች እና ከፍተኛ ሰልጣኝ መኮንኖች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝት አደረጉ
May 30, 2023 34
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) ፦የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አመራሮች እና ከፍተኛ ሰልጣኝ መኮንኖች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝት አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን መልዕክት የጽህፈት ቤታቸው ኃላፊ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ያቀረቡ ሲሆን፤ የአገር መከላከያ ሰራዊት በሁሉም አውዶች የአገርን ደህንነት እና ሉዓላዊነት ከጥቃት ለመጠበቅ ከሕዝብ አብራክ ወጥቶ ለሕዝብ እየኖረ ያለ የዜጎች አለኝታ በመሆኑ ላቅ ያለ ክብር የሚገባው ነው ብለዋል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና መከላከያ ሰራዊት የአገር እና የሕዝብ መከታ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ቡልቲ ታደሰ በበኩላቸው ኮሌጁ በሰው ኃይል ግንባታ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማር እና ስልጠናዎችን በመስጠት በሰው ኃይል ግንባታ ብቁ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ሰራዊቱ በዓለም ሰላም ማስከበር እና በሌሎች ተልኮዎች ውጤታማነቱን ማስመስከሩን ገልጸው ኮሌጁ በቀጣይም ስራውን በተሻለ ተግባር እንዲከውን የሚያስችል ስልጠና እየሰጠ ነው ብለዋል ። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት የፖለቲካ ሳይንስ መሪ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ዳር እስከዳር ታዬ “የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊስ ትናንት እና ዛሬ” በሚል የመወያያ ጽሑፍ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል። በውይይቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መሰጠቱን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በመዲናዋ በተለያዩ አካባቢዎች ህዝብን እያማረሩ ያሉ ህገ-ወጥ ጫኝና አውራጆች ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወስዷል- የአዲስ አበባ ሰላምና  ጸጥታ አስተዳደር  ቢሮ
May 30, 2023 47
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ህዝብን እያማረሩ ያሉ ህገ-ወጥ ጫኝና አውራጆች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ፤ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች በኢ-መደበኛ መንገድ የተደራጁ ጫኝና አውራጆች ከመጠን በላይ በማስከፈል እና ለህግና ስርዓት ተገዥ ባለመሆን ህዝብን እያማረሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ችግሩ በስፋት እንደሚስተዋል ገልጸው፤ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የ44 ማህበራት አባል የሆኑ 505 ጫኝና አውራጆች በህግ እንዲጠየቁ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በተገልጋይ ላይ ድብደባና ሌሎችም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ 97 ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡ በቀጣይም የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኃላፊዋ አረጋግጠዋል፡፡    
በመዲናዋ  ሕዝብና የጸጥታ መዋቅሩ ተቀናጅተው በመስራታቸው በሠላምና ጸጥታ ዙሪያ ለውጥ ተመዝግቧል-ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ
May 30, 2023 41
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) ፦በአዲስ አበባ ከተማ በለፉት ዘጠኝ ወራት ሕዝብና የጸጥታ መዋቅሩ በመቀናጀት በሰሩት ስራ በሠላምና ጸጥታ ዙሪያ ለውጥ መመዝገቡን የአዲስ አበባ ከተማ ሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከማዕከል እስከ ቀጠና ከሚገኙ አመራሮችና ኦፊሰሮች ጋር የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማና በወቅታዊ የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ነው።   የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ወንጀልን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። ሰላምና ደህንነት በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚቻለው በሕዝብ ተሳትፎ መሆኑን በመረዳት ነዋሪዎች በስፋት እንዲሳተፉ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ውጤቱ የተገኘው ህብረተሰቡን የሰላምና ደህንነት ባለቤት በማድረግ ተቀናጅቶ መስራት በመቻሉ ነው ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ የከተማዋን ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ በሁሉም የከተማ አካባቢዎች በርካታ የሰላም ሰራዊት ማደራጀት መቻሉን ተናግረዋል። ይህም አካባቢውን ይጠብቃል አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ለጸጥታ ሃይሉ ጥቆማ እንዲያደርግ ይደረጋል ብለዋል። በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ሰዎች በወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል ብለዋል። የሰላም ሰራዊቱ የሚመራበት ህግና ደንብ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። በመሆኑም በመዲናዋ ለሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የመንግስት፣ የሕዝቡና የጸጥታ አካላት ትብብር በተሻለ መጠናከሩን ተናግረዋል። ጽንፈኝነት ሠላምንና ደህንነትን እንዳያውክ ለማድረግ ነዋሪው አጠራጣሪ ነገሮችን እንደሚከታተል ገልጸዋል። በዚህ ሂደትም የታሰቡ እኩይ ሴራዎች መክሸፋቸውን ነው የተናገሩት።  
ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረት እና በታክስ ላይ የሚፈጸመውን ማጭበርበር ለመካለከል የቀረበው አዋጅ ጸደቀ
May 30, 2023 82
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባው ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረት እና በታክስ ላይ የሚፈጸመውን ማጭበርበር ለመከላከል የቀረበውን አዋጅ አጽድቋል፡፡ በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ ረቂቅ አዋጁን በተመለከተ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ በኢትዮጵያ መንግስት እና በግራንድ ዱቺ ኦፍ ሉዘምበርግ መንግስት መካከል በገቢ ላይ የሚከፈለውን ግብር በሚመለከት ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረት እና በታክስ ላይ የሚፈጸምን ማጭበርበር ለመከላከል የቀረበው ስምምነት የሁለትዮሽ ትብብርን ለማጠናከር የሚያስችል የህግ ማዕቀፍን የሚፈጥር ረቂቅ አዋጅ እንደሆነ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ ገልጸዋል፡፡ የውጭ የግል ካፒታል ፍሰት እና ኢንቨስትመንት በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ ወሳኝ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ሰብሳቢው፤ ስምምነቱ የሁለቱ ሀገራት ዜጎችን ብቻ ሳይሆን በሁለቱ ሀገሮች ነዋሪ የሆኑትንም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚስችል አዋጅ መሆኑን ለምክር ቤቱ አብራርተዋል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ከገንዘብ ሚኒስቴር የህግ አማካሪ ጋር በተለያዩ መድረኮች በረቂቅ አዋጁ አስፈላጊነት ላይ በሰፊው እንደተወያዩም አክለው ገልጸዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላትም፤ ረቂቅ አዋጁ በታክስ ማጭበርበር የሚታዩ ግድፈቶችን ለማረም የሚያስችል እና የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የሚያጠናክር አዋጅ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ምክር ቤቱ በውሎው ረቂቅ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1295/2015 አድርጎ በሙሉ ድምጽ ማጽደቁን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።
በሲዳማ ክልል ለአገራዊ ምክክሩ አጀንዳ መለየት የሚያስችል ስራ ተጀምሯል- የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን
May 29, 2023 100
ሃዋሳ ግንቦት 21 /2015 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ለአገራዊ ምክክሩ አጀንዳ መለየት የሚያስችለውን ስራ መጀመሩን የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች ተቋሙ እያከናወነ ያለውን ስራ አስመልክቶ ዛሬ በሃዋሳ ከተማ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ኮሚሽነር ዶክተር አምባዬ ኦጋቶ ፤ ኮሚሽኑ በያዘው እቅድ በሲዳማ ክልል በምክክር ሂደቱ የሚሳተፉ አካላትን በመምረጥ አጀንዳ መለየት የሚያስችለውን ስራ መጀመሩን ገልጸዋል። በዚህም ኮሚሽኑ ባዘጋጀው የተሳታፊዎች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰቢያ የአሰራር ስርዓት መሰረት ተሳታፊዎች ከወረዳዎች፣ከከተማ አስተዳዳሮችና ከክልሉ እንደሚመረጡ ተናግረዋል። ከወረዳ የሚመረጡ ተሳታፊዎች የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ ዘጠኝ የማህበረሰብ አደረጃጀቶች የተውጣጡ ሲሆኑ፣ ከየአደረጃጀቱ 50 ሰዎች ይለያሉ ብለዋል። በክልል ደረጃም ከሲቪክ ማህበራትንና ከሌሎችም የሚመለከታቸው ተቋማት የሚወከሉ እንደሚኖሩ ገልጸው፤ በክልሉ አራት ከተሞች ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት እንደሚደረግም ነው ዶክተር አምባዬ ያስረዱት። ሃዋሳ፣ይርጋለም፣በንሳና አለታ ወንዶ ከተወከሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ለመወያየት የተመረጡ ከተሞች መሆናቸውን ተናግረዋል። ተሳታፊዎች በሚለዩበት ወቅትም ልዩ ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ሴቶች፣ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች በበቂ መጠን እንደሚወከሉና ተሳትፎ እንደሚኖራቸውም ኮሚሽነሩ አስረድተዋል። የኮሚሽኑን ስራ የሚያግዙ ሰባት ተባባሪ አካላት በሂደቱ እንደሚሳተፉና በኮሚሽኑ አሰራር ላይ ስልጠና እንደሚወስዱ ጠቁመው፤ የተወከሉት አካላት በቂ ግንዛቤ ካገኙ በኋላ የአጀንዳ መረጣ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። ኮሚሽኑ የሚያካሂደው ውይይት ከታችኛው የሕብረተሰብ ክፍል የሚጀምርና የሕዝብ ምክክር እንደሚደረግበት ያመለከቱት ዶክተር አምባዬ፤ ስራውን ውጤታማ ለማድረግ መገናኛ ብዙሃን ተገቢውን መረጃ በመስጠት ህዝቡን ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ማድረግ አለባቸው ብለዋል። ኮሚሽነር ዶክተር ዮናስ አዳዬ በበኩላቸው፤ አገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር አብሮነትን ለማጠናከርና ለሀገር ግንባታ ከፍተኛ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። ኮሚሽነር ዶክተር ተገኝወርቅ ጌጡ፤ በተወሰኑ የኢትዮጵያ ክፍሎች በምክክሩ ተሳታፊ አካላትን በመምረጥ አጀንዳ የመለየት ስራ መጀመሩን ጠቅሰው፣ መላው የሲዳማ ክልል ሕዝብም በዚህ ታሪካዊ ሂደት በንቃት እንዲሳተፍ መልዕክት አስተላልፈዋል። ኮሚሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦችና በሐረሪ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳደደር የሀገራዊ ምክክር ተሳታፊዎችን በመምረጥ አጀንዳ መለየት የሚያስችለውን ስራ መጀመሩም ተገልጿል።  
ፖለቲካ
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አመራሮች እና ከፍተኛ ሰልጣኝ መኮንኖች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝት አደረጉ
May 30, 2023 34
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) ፦የመከላከያ ዋር ኮሌጅ አመራሮች እና ከፍተኛ ሰልጣኝ መኮንኖች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝት አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን መልዕክት የጽህፈት ቤታቸው ኃላፊ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን ያቀረቡ ሲሆን፤ የአገር መከላከያ ሰራዊት በሁሉም አውዶች የአገርን ደህንነት እና ሉዓላዊነት ከጥቃት ለመጠበቅ ከሕዝብ አብራክ ወጥቶ ለሕዝብ እየኖረ ያለ የዜጎች አለኝታ በመሆኑ ላቅ ያለ ክብር የሚገባው ነው ብለዋል።   የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና መከላከያ ሰራዊት የአገር እና የሕዝብ መከታ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ቡልቲ ታደሰ በበኩላቸው ኮሌጁ በሰው ኃይል ግንባታ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማር እና ስልጠናዎችን በመስጠት በሰው ኃይል ግንባታ ብቁ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ሰራዊቱ በዓለም ሰላም ማስከበር እና በሌሎች ተልኮዎች ውጤታማነቱን ማስመስከሩን ገልጸው ኮሌጁ በቀጣይም ስራውን በተሻለ ተግባር እንዲከውን የሚያስችል ስልጠና እየሰጠ ነው ብለዋል ። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት የፖለቲካ ሳይንስ መሪ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ዳር እስከዳር ታዬ “የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊስ ትናንት እና ዛሬ” በሚል የመወያያ ጽሑፍ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል። በውይይቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መሰጠቱን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በመዲናዋ በተለያዩ አካባቢዎች ህዝብን እያማረሩ ያሉ ህገ-ወጥ ጫኝና አውራጆች ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወስዷል- የአዲስ አበባ ሰላምና  ጸጥታ አስተዳደር  ቢሮ
May 30, 2023 47
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ህዝብን እያማረሩ ያሉ ህገ-ወጥ ጫኝና አውራጆች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ፤ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች በኢ-መደበኛ መንገድ የተደራጁ ጫኝና አውራጆች ከመጠን በላይ በማስከፈል እና ለህግና ስርዓት ተገዥ ባለመሆን ህዝብን እያማረሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ችግሩ በስፋት እንደሚስተዋል ገልጸው፤ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የ44 ማህበራት አባል የሆኑ 505 ጫኝና አውራጆች በህግ እንዲጠየቁ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በተገልጋይ ላይ ድብደባና ሌሎችም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ 97 ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡ በቀጣይም የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኃላፊዋ አረጋግጠዋል፡፡    
በመዲናዋ  ሕዝብና የጸጥታ መዋቅሩ ተቀናጅተው በመስራታቸው በሠላምና ጸጥታ ዙሪያ ለውጥ ተመዝግቧል-ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ
May 30, 2023 41
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) ፦በአዲስ አበባ ከተማ በለፉት ዘጠኝ ወራት ሕዝብና የጸጥታ መዋቅሩ በመቀናጀት በሰሩት ስራ በሠላምና ጸጥታ ዙሪያ ለውጥ መመዝገቡን የአዲስ አበባ ከተማ ሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከማዕከል እስከ ቀጠና ከሚገኙ አመራሮችና ኦፊሰሮች ጋር የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማና በወቅታዊ የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ነው።   የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ወንጀልን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። ሰላምና ደህንነት በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚቻለው በሕዝብ ተሳትፎ መሆኑን በመረዳት ነዋሪዎች በስፋት እንዲሳተፉ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ውጤቱ የተገኘው ህብረተሰቡን የሰላምና ደህንነት ባለቤት በማድረግ ተቀናጅቶ መስራት በመቻሉ ነው ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ የከተማዋን ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ በሁሉም የከተማ አካባቢዎች በርካታ የሰላም ሰራዊት ማደራጀት መቻሉን ተናግረዋል። ይህም አካባቢውን ይጠብቃል አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ለጸጥታ ሃይሉ ጥቆማ እንዲያደርግ ይደረጋል ብለዋል። በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ ሰዎች በወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል ብለዋል። የሰላም ሰራዊቱ የሚመራበት ህግና ደንብ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። በመሆኑም በመዲናዋ ለሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የመንግስት፣ የሕዝቡና የጸጥታ አካላት ትብብር በተሻለ መጠናከሩን ተናግረዋል። ጽንፈኝነት ሠላምንና ደህንነትን እንዳያውክ ለማድረግ ነዋሪው አጠራጣሪ ነገሮችን እንደሚከታተል ገልጸዋል። በዚህ ሂደትም የታሰቡ እኩይ ሴራዎች መክሸፋቸውን ነው የተናገሩት።  
ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረት እና በታክስ ላይ የሚፈጸመውን ማጭበርበር ለመካለከል የቀረበው አዋጅ ጸደቀ
May 30, 2023 82
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባው ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረት እና በታክስ ላይ የሚፈጸመውን ማጭበርበር ለመከላከል የቀረበውን አዋጅ አጽድቋል፡፡ በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ ረቂቅ አዋጁን በተመለከተ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ በኢትዮጵያ መንግስት እና በግራንድ ዱቺ ኦፍ ሉዘምበርግ መንግስት መካከል በገቢ ላይ የሚከፈለውን ግብር በሚመለከት ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረት እና በታክስ ላይ የሚፈጸምን ማጭበርበር ለመከላከል የቀረበው ስምምነት የሁለትዮሽ ትብብርን ለማጠናከር የሚያስችል የህግ ማዕቀፍን የሚፈጥር ረቂቅ አዋጅ እንደሆነ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ ገልጸዋል፡፡ የውጭ የግል ካፒታል ፍሰት እና ኢንቨስትመንት በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ ወሳኝ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ሰብሳቢው፤ ስምምነቱ የሁለቱ ሀገራት ዜጎችን ብቻ ሳይሆን በሁለቱ ሀገሮች ነዋሪ የሆኑትንም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚስችል አዋጅ መሆኑን ለምክር ቤቱ አብራርተዋል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ከገንዘብ ሚኒስቴር የህግ አማካሪ ጋር በተለያዩ መድረኮች በረቂቅ አዋጁ አስፈላጊነት ላይ በሰፊው እንደተወያዩም አክለው ገልጸዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላትም፤ ረቂቅ አዋጁ በታክስ ማጭበርበር የሚታዩ ግድፈቶችን ለማረም የሚያስችል እና የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የሚያጠናክር አዋጅ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ምክር ቤቱ በውሎው ረቂቅ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1295/2015 አድርጎ በሙሉ ድምጽ ማጽደቁን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።
በሲዳማ ክልል ለአገራዊ ምክክሩ አጀንዳ መለየት የሚያስችል ስራ ተጀምሯል- የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን
May 29, 2023 100
ሃዋሳ ግንቦት 21 /2015 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ለአገራዊ ምክክሩ አጀንዳ መለየት የሚያስችለውን ስራ መጀመሩን የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች ተቋሙ እያከናወነ ያለውን ስራ አስመልክቶ ዛሬ በሃዋሳ ከተማ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ኮሚሽነር ዶክተር አምባዬ ኦጋቶ ፤ ኮሚሽኑ በያዘው እቅድ በሲዳማ ክልል በምክክር ሂደቱ የሚሳተፉ አካላትን በመምረጥ አጀንዳ መለየት የሚያስችለውን ስራ መጀመሩን ገልጸዋል። በዚህም ኮሚሽኑ ባዘጋጀው የተሳታፊዎች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰቢያ የአሰራር ስርዓት መሰረት ተሳታፊዎች ከወረዳዎች፣ከከተማ አስተዳዳሮችና ከክልሉ እንደሚመረጡ ተናግረዋል። ከወረዳ የሚመረጡ ተሳታፊዎች የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ ዘጠኝ የማህበረሰብ አደረጃጀቶች የተውጣጡ ሲሆኑ፣ ከየአደረጃጀቱ 50 ሰዎች ይለያሉ ብለዋል። በክልል ደረጃም ከሲቪክ ማህበራትንና ከሌሎችም የሚመለከታቸው ተቋማት የሚወከሉ እንደሚኖሩ ገልጸው፤ በክልሉ አራት ከተሞች ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት እንደሚደረግም ነው ዶክተር አምባዬ ያስረዱት። ሃዋሳ፣ይርጋለም፣በንሳና አለታ ወንዶ ከተወከሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ለመወያየት የተመረጡ ከተሞች መሆናቸውን ተናግረዋል። ተሳታፊዎች በሚለዩበት ወቅትም ልዩ ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ሴቶች፣ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች በበቂ መጠን እንደሚወከሉና ተሳትፎ እንደሚኖራቸውም ኮሚሽነሩ አስረድተዋል። የኮሚሽኑን ስራ የሚያግዙ ሰባት ተባባሪ አካላት በሂደቱ እንደሚሳተፉና በኮሚሽኑ አሰራር ላይ ስልጠና እንደሚወስዱ ጠቁመው፤ የተወከሉት አካላት በቂ ግንዛቤ ካገኙ በኋላ የአጀንዳ መረጣ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። ኮሚሽኑ የሚያካሂደው ውይይት ከታችኛው የሕብረተሰብ ክፍል የሚጀምርና የሕዝብ ምክክር እንደሚደረግበት ያመለከቱት ዶክተር አምባዬ፤ ስራውን ውጤታማ ለማድረግ መገናኛ ብዙሃን ተገቢውን መረጃ በመስጠት ህዝቡን ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ማድረግ አለባቸው ብለዋል። ኮሚሽነር ዶክተር ዮናስ አዳዬ በበኩላቸው፤ አገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር አብሮነትን ለማጠናከርና ለሀገር ግንባታ ከፍተኛ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። ኮሚሽነር ዶክተር ተገኝወርቅ ጌጡ፤ በተወሰኑ የኢትዮጵያ ክፍሎች በምክክሩ ተሳታፊ አካላትን በመምረጥ አጀንዳ የመለየት ስራ መጀመሩን ጠቅሰው፣ መላው የሲዳማ ክልል ሕዝብም በዚህ ታሪካዊ ሂደት በንቃት እንዲሳተፍ መልዕክት አስተላልፈዋል። ኮሚሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦችና በሐረሪ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳደደር የሀገራዊ ምክክር ተሳታፊዎችን በመምረጥ አጀንዳ መለየት የሚያስችለውን ስራ መጀመሩም ተገልጿል።  
ማህበራዊ
ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና በሰዎች የመነገድ ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የባለድርሻ አካላት የትብብር ጥምረት ሊጠናከር እንደሚገባ ተጠቆመ
May 30, 2023 24
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ)፡- ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና በሰዎች የመነገድ ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የባለድርሻ አካላት የትብብር ጥምረት ሊጠናከር እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን በሚመለከት በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ ተግባራትን ማስፋት የሚያስችል አገር አቀፍ የልምድ ልውውጥ መድረክ ተካሂዷል። የልምድ ልውውጥ መድረኩ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና በአማራ ክልል መካከል የተከናወነ ሲሆን፤ በቀጣይም ወደ ሌሎች ክልሎች እንደሚሰፋም ተጠቁሟል፡፡   በመረሓ-ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የስራ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፣ የከተማዋ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተክሌ በዛብህ እና የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ገረመው ገብረፃዲቅ ተገኝተዋል። በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የምክር ቤት አባላት እንዲሁም የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ታድመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የስራ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፤ በኢትዮጵያ ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር፣ በሰዎች የመነገድና በህገ ወጥ መንገድ ለውጭ አገራት የስራ ስምሪት ዜጎችን የመላክ ተግባር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ በዚህም መንግስት የችግሩን አሳሳቢነት በመገንዘብ ዘርፈ ብዙ የመከላከልና የመቆጣጠር ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ነው ያሉት። ይህንን ተግባር በማጠናከር ረገድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘርፉ ከሚሰሩ አጋር አካላት ጋር የትብብር ጥምረት ማቋቋሙን አንስተዋል። ጥምረቱ በከተማዋ ፍትህ ቢሮ፣በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የተዋቀሩበት መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡ ጥምረቱ የሰዎች ዝውውር በስፋት የሚፈፀሙባቸው አካባቢዎችን በመለየት የቁጥጥርና የክትትል ስራዎች ማከናወን ዋነኛ ተግባሩ ስለመሆኑም አስረድተዋል። በተጨማሪም በጉዳዩ ላይ የማህበረሰቡን ግንዛቤ ማስፋትና ተጠያቂነትን ማስፈን ላይ እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡ በመሆኑም ይህንን የትብብር ጥምረት በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች በማስፋት ወንጀሉን ማስቆምና የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል። የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ተክሌ በዛብህ በበኩላቸው ከተማዋ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀል በሰፋት ከሚፈጸምባቸው አካባቢዎች መካከል አንዷ መሆኗን አንስተዋል፡፡ ወንጀሉ በህጻናትና በሴቶች ላይ ጎልቶ እየተፈጸመ መሆኑ ደግሞ ችግሩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ በሰዎች የመነገድ፣ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ የማሻገርና ህገ-ወጥ የስራ ስምሪትን በሚመለከት ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በመፈረም ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝም ጨምረው ገልጸዋል። የወንጀሉን አስከፊነትና በዜጎች ላይ የሚያደርሰውን አሉታዊ ተጽእኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት ተጠያቂነትን የማስፈን ስራ እየተከናወነ ስለመሆኑም አንስተዋል። ይሁን አንጂ እነዚህ ወንጀሎች አይነታቸውና ሁኔታቸው እየተቀያየረ የሚፈጸሙ በመሆናቸው የመከላከል ስራውን በተሻለ ቅንጅት ማከናወን ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በመሆኑም የተቋቋመውና በስራ ላይ ያለውን የትብብር ጥምረት አቅም ማሳደግና ወደ ሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች የማስፋትና የልምድ ልውውጥ የማድረግ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ገረመው ገብረጻዲቅ እንዲሁ በክልሉ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀል በስፋት እንደሚፈጸም ተናግረዋል፡፡ በዚህም ህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎችንና አካባቢዎችን በመለየትና ልዩ ክትትል በማድረግ ወንጀሉን የመከላከልና ተጠያቂነትን የማስፈን ስራው በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑም አብራርተዋል። ይሁን እንጂ ወንጀሉ የሚፈጸምበት ሁኔታ በእጅጉ ውስብስብ በመሆኑ የአጋር አካላት ድጋፍና እገዛ ያስፈልጋል ብለዋል። በመሆኑም ዛሬ በተደረገው የልምድ ልውውጥ የትብብር ጥምረትን ማቋቋም ያለው ጠቀሜታ የጎላ በመሆኑ ተግባሩን ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።  
በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ማህበራዊ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ጃፓን እንደምትደግፍ አምባሳደር ኢቶ ታካኮ ገለጹ
May 30, 2023 25
ዲላ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ማህበራዊ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የጃፓን መንግስት እንደሚደግፍ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ ገለጹ። በጌዴኦና ምዕራብ ጉጂ ዞኖች አጎራባች አካባቢዎች ማህበራዊ ልማትና መስተጋብርን የሚያጎለብት ፕሮጀክት ዛሬ በዲላ ከተማ ይፋ ሆኗል። ፕሮጀክቱ ከጃፓን መንግስት በተገኝ 83 ሚሊዮን ብር ድጋፍ በቀጣይ ሦስት ዓመታት በዞኖቹ ባሉ አራት አጎራባች ወረዳዎች የሚተገበር መሆኑም ተመላክቷል። በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ ፕሮጀክቱ ይፋ ሲደረግ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ማህበራዊ ልማትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማገዝ የጃፓን መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል።   በተለይ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም መሰረት ይጥላል ተብሎ ለሚጠበቀው ለኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን የ3 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ መደረጉንም ለአብነት አንስተዋል። ዛሬ በሁለቱ ዞኖች አጎራባች አካባቢዎች ይፋ የተደረገው ፕሮጀክት የዚህ ድጋፍ አካል መሆኑን ጠቅሰው፣ "ፕሮጀክቱ ለሰላም ግንባታ፣ ለማህበራዊ ኑሮ መሻሻልና ለማህበራዊ ትስስር ጠቀሜታው የጎላ ነው" ብለዋል። በተለይ አጎራባች አካባቢዎችን በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላም ከማስፈን ባለፈ ሴቶችና ወጣቶች ኑሯቸውን ሊያሻሽሉ በሚችሉ ስራዎች እንዲሳተፉ የፋይናንስ ድጋፍ እንደሚደረግ አመላክተዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላምና ማህበራዊ ልማት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በጃፓን መንግስት በኩል መሰል ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በሁሉቱ ዞኖች አጎራባች አካባቢዎች ከዚህ ቀደም የነበረው የጸጥታ ችግር ሙሉ በሙሉ ተፈትቶ ህብረተሰቡ ፊቱን ወደልማት ማዞሩን ያነሱት ደግሞ በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ ጉጂ ዞን የፀጥታ አስተዳደር የግጭት ፈጥኖ ምላሽ አስተባባሪ አቶ አየለ ወላሳ ናቸው። በዞኑ ገላናና ቡሌ ሆራ ወረዳዎች በተደጋጋሚ የሚከሰተውን የድርቅና የጎርፍ አደጋ ችግሮች ለማቃለል የማህበረሰብ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም መጀመሩ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፕሮጀክቱ በአካባቢው የልማትና የማህበራዊ መስተጋብርን በሚያጎለብት መልኩ ተፈጻሚ እንዲሆን በዞኑ በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግም ተናግረዋል። በደቡብ ክልል የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ክትትል አስተባባሪ አቶ ከፍያለው ቢሬ በበኩላቸው፣ ሁለቱን ዞኖች በመሰረተ ልማትና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነታቸውን በማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው ፕሮጀክት ይህንን ከማጠናከር ባለፈ ህብረተሰቡ ሰርቶ እንዲለወጥ የፋይናንስ ድጋፍና ስልጠና በመስጠት የማህበረሰቡን ኑሮ ለማሻሻል አስተዋጾው የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመድረኩ የጃፓን ኤምባሲና የሁለቱ ዞኖች የሥራ ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ፕሮጀክቱ ከ40 ሺህ በላይ አባወራና እማወራዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ተገልጿል።  
በምዕራብ ወለጋ ዞን በበጀት ዓመቱ በተለያዩ የልማት መስኮች ስኬታማ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መከናወኑ ተገለጸ
May 30, 2023 22
ግምቢ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ወለጋ ዞን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በተለያዩ የልማት መስኮች ስኬታማ የበጋ ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መከናወኑን የዞኑ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ትብብር ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የዞኑ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ትብብር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተገኝ ቀኖ ለኢዜአ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በተለያዩ መስኮች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሲከናወን ቆይቷል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተካሄደ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራም ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ መከናወኑን ገልጸዋል። የዞኑ በጎ ፈቃደኞች ከ45 በላይ በሆኑ የልማት ዘርፎች ተሳትፎ ማድረጋቸውን ገልጸው፤ በዚህም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። ከእነዚህም፤ በመንግስትና በበጎ ፈቃደኛ ባለሀብቶች ትብብር 136 አነስተኛ ድልድዮች መሰራታቸውንና የ290 የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳትና አዲስ ግንባታ ስራ መከናወኑን እንደ አብነት አንስተዋል።   በዞኑ ለሚገኙ ትምህርት ቤቶችና ቤተ-መጻህፍት የሚውሉ የተለያዩ ይዘት ያላቸው ከ95 ሺህ በላይ መጻህፍት ከበጎ ፈቃደኞች መሰብሰቡንም አክለዋል። በተጨማሪም በዞኑ ገጠር አካባቢዎች 300 የመምህራን ቤቶች እድሳት እንዲሁም የቅድመ መደበኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ መከናወኑን ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪዎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍና የደም ልገሳም በበጎ ፈቃደኞቹ የተከናወኑ ስራዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።   በበጎ ፈቀደኞች የተሰሩ የልማት ስራዎችም መንግስት ለሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች አጋዥ በመሆናቸውም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው መሆኑን አስገንዝበዋል። በመጪው ክረምትም የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ የዜግነት የበጎ ፈቃድ ስራዎች ተጠናክረው የሚከናወኑ እንደሆነም ተናግረዋል። በበጎ ፈቃድ ስራው እየተሳተፉ ካሉ የዞኑ ነዋሪዎች መካከል የግምቢ ከተማ ነዋሪው ሼህ ሀሰን መሓመድ በበጎ ፍቃድ ስራው የህሊና እርካታ ማግኘታቸውን ገልጸው ሌሎችም በበጎ ፈቃድ ስራ እንዲሳተፉ ጠይቀዋል። ሌላው ተሳታፊ አቶ አብደላ አብዱ በበኩላቸው ከሌሎች ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን ለአቅመ ደካሞችና አካል ጉዳተኞች የአልባሳት ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በመጪው ክረምት ከሌሎች ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለመሳተፍ ዝግጅት ላይ እንደሆኑ ገልጸዋል።
በወይዘሪት ፀጋ በላቸው ላይ ከተፈጸመው የጠለፋ ወንጀል ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
May 30, 2023 47
ሀዋሳ ግንቦት 22 / 2015 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ በወይዘሪት ፀጋ በላቸው ላይ ከተፈጸመው የጠለፋ ወንጀል ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቀ።   የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ የከተማችን ነዋሪ በሆነችው ወይዘሪት ፀጋ በላቸው ላይ የደረሰባትን የጠለፋ ወንጀል ቤተሰቦቿ ግንቦት 15 ቀን 2015 ዓ.ም ለፖሊስ አቤቱታ አቅርበዋል ብለዋል። በዚህም የፖሊስ መምሪያው ተፈጸመ በተባለው የወንጀል ድርጊት መሰረት ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ብርቱ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በሂደቱም የጸጥታ ሀይሉ ባደረገው ክትትል ከወይዘሪት ፀጋ በላቸው የጠለፋ ወንጀል ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ መጀመሩን አብራርተዋል። የችግሩን አሳሳቢነት በመገንዘብ መምሪያው ከሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ጭምር አስፈላጊውን ጥረት እያደረገም እንደሚገኝ በመግለጫቸው አመላክተዋል። ሁሉም ሰው ከህግ በታች በመሆኑ የወንጀሉ ፈጻሚን በቁጥጥር ስር ለማዋል የተቀናጀ ስራ እየተሰራ መሆኑን አመላክተው፤ በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚሰራጩ አሉባልታዎች ህብረተሰቡ መደናገር እንደሌለበትም አስገንዝበዋል። ህብረተሰቡ ፖሊስ የሚያደርገውን ክትትል መረጃ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። የፀጥታ አካላትና ፖሊስ ተጠርጣሪው ሣጅን የኋላ መብራቴ እና የተጠለፈችውን ወይዘሪት ፀጋ በላቸው ይዞ ከተሰወረበት ቦታ አድኖ ለመያዝ የሚያደርገውን ጥረት ህብረተሰቡ እንዲያግዝ ጠይቀዋል። በመሆኑም 09 64 50 46 77 እና 09 69 41 52 72 ስልክ ቁጥሮች ህብረተሰቡ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።   የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ በበኩላቸው የጸጥታ ሀይሉ አቤቱታው ከደረሰበት ዕለት አንስቶ ወንጀሉን የፈጸመውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ለማዋል የተቀናጀ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በተለይም ተጠርጣሪው ይኖርበታል ተብሎ በሚገመትባቸው ቦታዎች የጸጥታ ሀይል የተሰማራ መሆኑን ጠቁመው፤ ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚያስችል ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን አብራርተዋል። ተጠርጣሪው ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሸሽቶ በክልሉ የተሰወረባቸውን አካባቢዎችና ከአጎራባች ክልሎች የጸጥታ ሀይሎች ጋር የተቀናጀ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። ወንጀል ፈጻሚውን ግለሰብ በተቀናጀ መንገድ ከቁጥጥር ስር ለማዋል የጸጥታ ሀይል ያለዕረፍት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው የሚደረገውን ጥረት ማህበረሰቡ እንዲደግፍ አሳስበዋል።
ኢኮኖሚ
በመዲናዋ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትና የአገልግሎት መቆራረጥ ችግርን ለመቀነስ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ነው- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
May 30, 2023 28
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና የአገልግሎት መቆራረጥ ችግርን ለመቀነስ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። በአዲስ አበባ ከተማ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና አገልግሎት መቆራረጥ ችግርን ለመቅረፍ የፌዴራል እና የከተማ አስተዳድሩ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች በተገኙበት ውይይት ተካሄዷል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ አዲስ አበባ የዲፕሎማሲ ማዕከል እና ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ፍሰት ያለባት ከተማ በመሆኗ፤ ደረጃዋን የሚመጥን የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል። በሰው ሰራሽና በተፈጥሯዊ ምክንያቶች በመሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርስን ጉዳት በኃይል አቅርቦት ላይ መቆራረጥ እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል። የኃይል መቆራረጥ በንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ላይም ጫና እያሳደረ መሆኑን ገልጸው፤ ከተማ አስተዳድሩ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማስፋፋት የሚያስችሉ መሰረተ ልማቶችን እያስፋፋ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ በበኩላቸው አዲስ አበባን ጨምሮ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማሻሻል አስቻይ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በአዲስ አበባ ከመሰረተ ልማት እድገቷ ጋር ተያይዞ የኤሌክትሪክ ፍላጎትን ለማሳደግና ለማዘመን ከፍተኛ በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። ለአብነትም ከሰው ንክኪ ነጻ ቆጣሪዎችን ለኢንዱስትሪ ደንበኞች መቅረቡን እና ደንበኞች ቅሬታቸውን በቴክኖሎጂ ተጠቅመው በማኅበራዊ ሚዲያ የሚያቀርቡበት ስርዓት መዘጋቱን አንስተዋል። በሌላ በኩል የአገልግሎት ለማሳለጥና ከከተማ አስተዳድሩ ጋር በቅርበት ለመስራት ያልተማከለ አደረጃጀት መፍጠሩንም ነው አቶ ሽፈራው ያስረዱት። የኃይል መቆራረጥ ችግር ከመቅረፍ ባሻገር የኃይል አቅርቦት እና አገልግሎት ተደራሽ ባልሆነባችው የመዲናዋ አካባቢዎች አገልግሎቱን ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በምክክር መድረኩ ላይ የዘርፉን ችግሩን ለማቃለል የሚያስችል የ90 ቀናት እቅድ የሚያወጣ ቡድን ተቋቁሟል።
ከሀገር ውስጥ የስኳር ምርት በተጨማሪ 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት ዝግጅት ተደርጓል- የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር
May 30, 2023 21
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015(ኢዜአ)፡- ከሀገር ውስጥ የስኳር ምርት በተጨማሪ 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት መንግስት በዝግጅት ላይ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የበጀት ምንጫቸውን ለብሔራዊ ባንክ አሳውቀው በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን ከውጭ እንዲያስገቡ ከተፈቀድላቸው ባለኃብቶች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ የዘይት፣ ስኳር እና ሌሎችም መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች እጥረትና የዋጋ ንረት ለመቆጣጠር መንግስት ለሀገር ውስጥ ባለኃብቶች ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ ይታወቃል፡፡ በዚህም ባለፉት አስር ወራት 411 አስመጭዎች በፍራንኮ ቫሉታ የተሳተፉ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የዘይት አቅርቦት 85 በመቶ መሸፈን ተችሏል፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በልሁ፤ መንግስት የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ፍራንኮ ቫሉታ በመፍቀድና በመሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች በታክስ መልክ ያገኘው የነበረውን 10 ቢሊየን ብር አጥቷል፡፡ በፍራንኮ ቫሉታ የሚሳተፉ አስመጭዎችን አገልግሎት ከማሳለጥ ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶች በበቂ ሁኔታ እንዲቀርቡ ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥሯል ብለዋል፡፡ በመሆኑም መንግስት ለአምስት የአገር ውስጥ የተጣራ ዘይት አምራች ድርጅቶች የማምረት አቅማቸውን ታሳቢ በማድረግ 50 ሚሊየን ዶላር እንደመደበላቸው ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል በሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች 650 ኩንታል ስኳር ተመርቶ ለገበያ እየቀረበ መሆኑን ጠቅሰው፤ በስኳር ኮርፖሬሽን በኩል ተጨማሪ 2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ለአብነት በፍራንኮ ቫሉታ በአማካኝ በ342 ብር ወደ አገር ወስጥ የሚገባ ባለ አምስት ሊትር ዘይት የተለያዩ የግብይት ሰንሰለቶችን አልፎ ለሸማቹ እስከ 1 ሺህ ብር በሚደርስ የተጋጋነ ዋጋ እየቀረበ መሆኑ ተገልጿል። በመሆኑም በፍራንኮ ቫሉታ ምርታቸውን ወደ ሀገር ውስጥ ለሚያስገቡት አስመጭዎች ቀጥታ ከሸማቹ ጋር እንዲገናኙ የቅዳሜና እሁድ ገበያን ማስፋት እንደ አማራጭ ተይዟል ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባና በክልሎች እስከ 1 ሺህ ነጋዴዎችና ሸማቾች በቀጥታ የሚገናኙበት የቅዳሜና እሁድ የገበያ ሰንሰለት ለመፍጠር መልካም ጅምር ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና የዋጋ ንረትን ለመግታት አቅርቦትና ፍላጎቱን የማመጣጠንና ስርጭቱን ፍትሃዊ የማድረግ ስራ በስፋት ይከናወናል በማለት ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከብሔራዊ ባንክ ዶላር የሚያገኙ ድርጅቶች ከስምንት በመቶ በላይ ትርፍ እንዳያሰሉ መደረጉን ለአብነት ጠቅሰዋል። በፍራንኮ ቫሉታም ሆነ በማንኛውም መንገድ ከውጭ ያስገቡትን ምርት መጋዘን ውስጥ ማከማቸት በህግ ያስጠይቃል፤ መንግስትም ተከታትሎ እርምጃ ይወስዳል ሲሉ አረጋግጠዋል።      
የብልፅግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አመራርና ሠራተኞች የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽንን ጎበኙ
May 30, 2023 32
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015(ኢዜአ)፡- የብልፅግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አመራርና ሠራተኞች በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽን ጎበኙ። "ከቤተ-ሙከራ ወደ አዝመራ" በሚል መሪ ሃሳብ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀው የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽን ሚያዝያ 29 ቀን 2015 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተመርቆ ለተመልካቾች ክፍት መደረጉ ይታወቃል። በአውደ-ርዕዩ ላይ በግብርናው ዘርፍ የተገኙ የተለያዩ ስኬቶችን የሚያሳዩ የምርምርና የፈጠራ ሥራዎች፣ ዲጂታላይዜሽንና የግብርና ፋይናንስ ላይ ያተኮሩ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ ቀርበዋል። በዚህም የተለያዩ ተቋማት ሠራተኞች፣ አርሶ አደሮች፣ በተለያዩ የክፍል ደረጃ ያሉ ተማሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎችም ጎብኝተዋል። በዛሬው እለትም የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት አመራርና ሠራተኞች አውደ-ርዕዩን ጎብኝተዋል። የብልፅግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ግርማ ወርቁ፤ በጉብኝቱ የግብርናውን ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ አስደናቂ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን ተመልክተናል ብለዋል። በከተማዋ የተጀመረውን የሌማት ትሩፋት የተሳካ ለማድረግ የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የማስተዋወቅ ሥራ እንሰራለን ነው ያሉት። ከጉብኝቱ ታዳሚዎች መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው የጽህፈት ቤቱ ሠራተኞች በአውደ-ርዕዩ በተመለከቱት መደነቃቸውን ጠቅሰው፤ በግብርና ዘርፍ አገሪቷ የጀመረቻቸው ሥራዎች ለስኬት እንደሚበቁም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። የግብርና የሚኒስትሩ አማካሪ ማርቆስ ሌራንጎ ፤ የኤግዚቢሽኑ መዘጋጀት ዋና ዓላማ የግብርናውን ዘርፍ ከኋላቀር አሠራር ለማላቀቅ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት ለሳይንስ ውጤቶች ትኩረት እንዲሰጡ ለማስገንዘብ ነው ብለዋል። በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የዘርፉን ባለድርሻ አካላት ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ኤግዚቢሽኑን እየጎበኙ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ ቀናት ሌሎችም እንዲጎበኙ ጥሪ አቅርበዋል። ኤግዚቢሽኑ ለሕዝብ ዕይታ ክፍት ከተደረገ ጀምሮ እስካሁን ከ45 ሺህ በላይ ዜጎች የጎበኙት መሆኑ ታውቋል።
ዩኒቨርሲቲው በ22 ሚሊዮን ብር  ወጪ ያስገነባውን የመኖ ማቀነባበሪያ ሥራ አስጀመረ
May 30, 2023 30
ደሴ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) ፡- ወሎ ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል አምስት ዞኖች ያለውን የእንስሳት መኖ እጥረት ለማቃለል በ22 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባውን የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ሥራ አስጀመረ። ማቀነባበሪያው በአማራ ክልል በደቡብና ሰሜን ወሎ፣ በሰሜን ሸዋ፣ ዋግ ኸምራ እና ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች መኖን ተደራሽ ለማድረግ የሚያግዝ ሲሆን፤ በቀን 360 ኩንታል መኖ የማምረት አቅም እንዳለውም ተገልጿል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር መንገሻ አየነ ማቀነባበሪያውን ሥራ ለማስጀመር ዛሬ በተዘጋጀ ሥነ ስርአት ላይ እንዳሉት፣ ተቋሙ ከመማር ማስተማርና ምርምር ባሻገር በማህበረሰብ አገልግሎት ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ነው። በዞኖቹ ያለውን የእንስሳት እርባታና ማድለብ ሥራ አጠናክሮ ለማስቀጠል ማነቆ የሆነውን የእንስሳት መኖ እጥረት ችግር ለማቃለል በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። ለእዚህም ዩኒቨርሲቲው በ22 ሚሊዮን ብር ያስገነባው የመኖ ማቀነባበሪያ ዛሬ ሥራ መጀመሩን ነው ፕሬዚዳንቱ ያስታወቁት። እንደፕሬዚዳንቱ ገለጻ በቀጣይም ተጨማሪ የመኖ ማቀነባበሪያ በመገንባት ጥራት ያለው መኖ በብዛትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ ለማቅረብ ይሰራል። የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ፋሪስ ኃይሉ በበኩላቸው "በምንሰጠው የማህበረሰብ አገልግሎት የኅብረተሰቡን ችግር በጥናትና በምርምር ጭምር ታግዞ ለመፍታት እየሰራን ነው" ብለዋል። በዞኖቹ ለእንስሳት ሀብት ልማት ያለውን ተስማሚነትና ተግዳሮት ለመለየት በተደረገ ጥረት የእንስሳት መኖ እጥረትና ጥራት መጓደል እንዳለ በጥናት መረጋገጡን ተናግረዋል። በዚህም ለህብረተሰቡ መኖ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ዩኒቨርሲቲው ማቀነባበሪያውን መገንባቱን ገልጸዋል። የመኖ ማቀነባበሪያው በቀን 360 ኩንታል መኖ እንደሚያመርት የተናገሩት ደግሞ የዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ሕክምና ትምህርት ቤት ዲን ዶክተር ታረቀኝ ትንታጉ ናቸው። እንደ ዲኑ ገለጻ ማቀነባበሪያው በዋናነት ለከብቶች ማድለብ፣ ለወተት ላም፣ ለእንቁላል ጣይ ዶሮ እና ለዶሮ ጫጩት የሚሆን መኖ ያመርታል። ምርቱን በተመጣጣኝ ዋጋ ለኅብረተሰቡ ለማድረስም ደሴ፣ ኮምቦልቻ እና ሐይቅ ከተሞች ላይ የመኖ ማከፋፈያ ቅርንጫፎች እንደሚከፈቱ ዶክተር ታረቀኝ አስታውቀዋል። በደሴ ከተማ በወተት ላም እርባታ ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል ወጣት ይመር ዓሊ በሰጠው አስተያየት በአካባቢያቸው በቂና ጥራት ያለው መኖ ባለማግኘታቸው ላሞቹንና ጥጆቹን ለመመገብ ሲቸገር እንደነበር ገልጿል። ዝርያቸው የተሻሻሉ ላሞችን ቢያረባም በመኖ እጥረት በሚፈለገው ልክ ወተት ለማግኘት እንዳልቻለ ገልጾ፣ በዩኒቨርሲቲው የተገነባው ማቀነባበሪያ ችግሩን ይፈታል የሚል እምነት እንዳደረበት ተናግሯል። በማቀነባበሪያው ሥራ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ላይ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢትዮጵያን ወክለው በ7ኛው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ፍጻሜ ውድድር የተሳተፉ ተማሪዎች ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ
May 29, 2023 88
አዲስ አበባ ግንቦት 21/2015(ኢዜአ)፦ በ7ኛው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ፍጻሜ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉት ተማሪዎች ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። ውድደሩ ከግንቦት 16 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2015 በቻይና ሼንዘን ከተማ የተካሄደ ሲሆን በውድድሩ ከ36 አገሮች የተውጣጡ 146 ቡድኖች ተሳትፈዋል፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ተማሪዎቹ እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን በመሆን በፕራክቲካል ትራክ (ዳታኮም፣ሴኪዩሪቲ፣ገመድ አልባ የኮምፒዩተር ኔትወርክ ፣ ቢግ ዳታ፣ ስቶሬጅ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ‘OpenEuler’ እና ‘OpenGauss’ የተሰኙ የመረጃ ቋትና የአሰራር ስርዓቶችን ያካትታል) ሁለት ቡድን እና አንድ ቡድን በኢኖቬሽን ትራክ ላይ ተሳትፈዋል።   በኢኖቬሽን ትራክ የተወዳደሩት ተማሪዎች “የግዕዝ ፊደላት ክላሲፋየር” የተሰኘ የፈጠራ ስራ መወዳደሪያ ይዘው መቅረባቸውን የትምህርት ሚኒስቴር በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መረጃ አመልክቷል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ውጤቱ ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች በሌሎችም ዘርፎች በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉ ያሳየ ነው ብለዋል። የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርትን ጥራት ለማረጋገጥ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆነው አገርን የሚያስጠሩ ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁዋዌ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሊዩ ጂፋን ተማሪዎቹ ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን ገልጸው ድርጅቱ የአይሲቲ ዘርፉን ለማጠናከርና ተተኪዎችን ለማፍራት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አመልክተዋል። ተማሪዎቹ በውጤታቸው መደሰታቸውንና ውድድሩ የሁዋዌን ዋና መስሪያ ቤት ከመጎብኘት አንስቶ ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ያገኙበት መሆኑን ተናግረዋል። ተማሪዎቹ በዓለም አቀፍ ውድድሩ ላይ የተሳተፉት የአገር ውስጥ ማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍና በአገር አቀፍና አህጉራዊ ውድድሮች በማሸነፋቸው እንደሆነ ተገልጿል። በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ተማሪዎች ከጎንደር፣ ዋቸሞ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲዎች የተገኙ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።          
ኢትዮ ቴሌኮም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ስማርት የመማሪያ ክፍል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  ስራ አስጀመረ
May 26, 2023 127
  አዲስ አበባ ግንቦት 18/2015 (ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ስማርት የመማሪያ ክፍል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማቋቋም ዛሬ በይፋ ስራ አስጀምሯል። ኢትዮ-ቴሌኮም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ስማርት የመማሪያ ክፍሎችን ለማስረጽ የሚያስችለውን ተግባር ለማከናወን ከትምህርት ሚኒስቴርና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። በስምምነቱ መሰረት ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራት ኪሎ ካምፓስ ያስገነባው የመማሪያ ክፍል ስራ ጀምሯል። በኩባንያው እውን የሆነው የስማርት መማሪያ ክፍሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸው መሆኑ ተገልጿል። ይህም የመማር ማስተማሩን ሂደት ከተለመደው አካሄድ በተሻለ ቀላል እንደሚያደርገው የተጠቆመ ሲሆን በዚህም ተማሪዎች ከልማዳዊ ትምህርት በማለፍ በተግባራዊ ተሞክሮ የበለጸገና የተሻለ የትምህርት ተሞክሮ እንዲኖራቸው ያስችላቸዋል ተብሏል። የስማርት ክፍሉ መምህራን በቀላሉ ማስተማር እንዲችሉ እንዲሁም የንድፈ ሃሳብ ትምርቶችን በቴክኖሎጂ ቤተ-ሙከራ እንዲደገፉ ያስችለዋል ነው የተባለው። ይህም የተማሪዎችን ሁኔታ ለመከታተል ፣የምዘና ፈተናዎችን ለማረምና ውጤቶችን ለማሳወቅ እንደሚያስችል ተመላክቷል።
ሶስተኛው አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የመዝጊያ መርሐ-ግብር በመካሄድ ላይ ነው
May 26, 2023 132
አዲስ አበባ ግንቦት 18 ቀን 2015 (ኢዜአ) ፡- "ክህሎት ለተወዳዳሪነት" በሚል መሪ ሀሳብ ላለፋት 5 ቀናት ሲካሄድ የቆየው ሶስተኛው አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የመዝጊያ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው። በስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት በተካሄደው የውድድር መድረኩ 267 የሚሆኑ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች በተለያዩ ዘርፎች የክህሎት ውድድር አካሂደዋል፡፡ በውድድሩም በቴክኒክና ሙያ ተቋማት አሰልጣኞች፣ ሰልጣኞች እና ኢንተርፕራይዞች የተሰሩ ከ103 በላይ የተለያዩ የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ቀርበው ተጎብኝተዋል፡፡ ከ10 ያላነሱ የዘርፉ ተግዳሮቶች ላይ ያተኮሩ ተግባራዊ የጥናትና ምርምር ሥራዎች እና የፓናል ውይይቶችም ተካሂደዋል፡፡ በተጨማሪም በሞዴል ኢንተርፕራይዞች የተመረቱ ሀገር በቀል ምርቶችም በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች ቀርበው ግብይት ተከናውኗል፡፡ የተሻለ ውጤት ላመጡ ተወዳዳሪዎች የሽልማትና የእውቅና መርሐግብር እንደሚካሄድም ተገልጿል። በመዝጊያ ስነ-ስርዓቱ ላይ የስራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።  
ስምንተኛው ሃገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ነገ በአሶሳ ይጀመራል
May 25, 2023 166
አሶሳ ግንቦት 17 /2015 (ኢዜአ) ፡- ስምንተኛው ዓመታዊ ሃገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ነገ እንደሚጀመር የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ። ኮንፍረንሱ “የምርምርና ዩኒቨርሲቲ ትስስር ለዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ሀሳብ እንደሚካሄድ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር አብዱልሙሃሰን ሃሰን ዛሬ ለኢዜአ ገልጸዋል። ዓላማው ተመራማሪዎች ምርምራቸውን በማቀናጀት ለሃገር ዘላቂ ልማት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ለማጠናከር መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት የሚካሄደው ኮንፍረንሱ እስከ ግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም. እንደሚቆይ ጠቁመው፤ ከአዲስ አበባ፣ ጎንደር ፣ሃሮማያና ጅማን ጨምሮ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ይሳተፋሉ ብለዋል፡፡ በዚህ ሀገር አቀፍ ኮንፍረንስ 25 ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው የሚጠበቅ መሆኑን ዶክተር አብዱልሙሃሰን አስታውቀዋል። ጥናታዊ ጽሁፎቹ በኢንጂነሪንግና ተክኖሎጂ፣ በተፈጥሮ፣ በጂኦሎጂ፣፣ በግብርና፣ በቢዝነስ፣ በኢኮኖሚክስ፣ በማህበራዊ ሳይንስና ሌሎችም ዘርፎች ላይ እንደሚያተኩሩ ጠቁመዋል፡፡ ሰባተኛው ሃገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስም በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት መካሄዱንና ይህም ሳይንሳዊ እውቀቶች በመለዋወጥ ተቀናጅተው መስራት ያስቻለ ግንዛቤ ተገኝቶበት እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በስምንተኛው ኮንፍረንስም የሚቀርቡ ጽሁፎች ዩኒቨርሲቲዎች የትምህርትና የልህቀት ማዕከላትን የመደገፍ ሃገራዊ የትኩረት አቅጣጫን በማገዝ ምርምሮች ወደ ተግባር የሚቀየሩበትን ተሞክሮ የሚያሳድጉ መግባባቶች ይደረስበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስረድተዋል፡፡      
ስፖርት
የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የስፖርት ጆርናል ድረ-ገጽ በይፋ አስመረቀ
May 30, 2023 37
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በዘርፉ የሚካሄዱ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ተደራሽ የሚያደርግ የስፖርት ጆርናል ድረ -ገጽ በይፋ አስመረቀ፡፡ አካዳሚው ድረ- ገጹን ይፋ ያደረገው ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆየው 8ተኛው ሀገር አቀፍ የስፖርት ምርምር ጉባኤ ላይ ነው። የአካዳሚው የጥናትና ምርምር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አመንሲሳ ከበደ፤ድረ-ገጹ የሀገሪቱ የስፖርት ተመራማሪዎች የምርምር ሥራቸውን ለማቅረብ እንዲችሉ እድሉን የሚያመቻች ነው ብለዋል። በዋናነትም በዘርፉ የሚካሔዱ ጥናትና ምርምሮችን ለሁሉም አካላት ተደራሽ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል። በድረ ገጹ ላይ ከሀገር ውስጥም ሆነ ሌሎች አካላት ተቀድተው ወይም ቀጥታ ተገልብጠው የመጡ ጥናቶችን ለመለየት የሚያስችል መተግበሪያ የያዘ መሆኑንም አስረድተዋል። ይኸም በአብዛኛው የሚቀርቡ ጥናቶች መደርደሪያ ላይ ከመታየት ባለፈ ተደጋጋሚነት ያላቸው በመሆኑም ይሕንኑ ለማጣራትና አዳዲስ ምርምሮችን እንዲካሔዱ ለማድረግ የሚያበረታታ ነው ብለዋል።   ድረገጹ ሀገር በቀል ዕውቀቶች እንዲሰፉና ሳይንሳዊ ይዘት እንዲኖራቸው ከማድረግ ባለፈ የሀገሪቱን ስፖርት በጥናትና ምርምር ለማሳደግ ፋይዳው የጎላ እንደሆነም ገልፀዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ለመሥራት የሚጠቅሙ የስፖርት ምርምር ቤተ ሙኩራ አጠቃቀም የልኬት መመሪያ ማዘጋጀቱን ገልፀዋል። በዚህም አካላዊ ልኬት፣ የልብ ሥርዓት ኡደት ልኬት፣ የደም ናሙና ልኬት፣ የብቃት ልኬት፣ የሥነ-ልቦና ልኬት፣ የብቃት አመልካች ልኬቶችና የብሔራዊ ቡድኖች አባላት የቅድመ ምርመራ አገልግሎቶችን እየሰጠ ነው ብለዋል።      
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ
May 29, 2023 70
አዲስ አበባ ግንቦት 21/2015(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋሉ። በመርሐ-ግብሩ መሰረት ኢትዮጵያ መድን ከወልቂጤ ከተማ ከቀኑ ዘጠኝ ሰአት ላይ ይጫወታሉ። በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ኢትዮጵያ መድን በ45 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን ወልቂጤ ከተማ በ29 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ኢትዮጵያ መድን በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ የሊጉ ጨዋታዎች በሁለቱ አሸንፎ በአንዱ ተሸንፎ በሁለቱ አቻ ወጥቷል። በአንጻሩ ወልቂጤ ከተማ ካለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። ሁለት ጊዜ ተሸንፎ በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ አቻ ወጥቷል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያ ዙር ያደረጉት ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን 2 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። በ26ኛ ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር የመጨረሻው ጨዋታ በሀዲያ ሆሳዕና እና ኢትዮጵያ ቡና መካከል ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ይደረጋል። ሀዲያ ሆሳዕና በ36 ነጥብ 5ኛ ደረጃን የያዘ ሲሆን ኢትዮጵያ ቡና በ35 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሀዲያ ሆሳዕና ካለፉት አምስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በአንዱ ተሸንፎ ሶስት ጊዜ አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። ሁለት ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር ያደረጉት ጨዋታ ሀዲያ ሆሳዕና 1 ለ 0 ማሸነፉ ይታወሳል። ትናንት የሲዳማ ቡና እና ወላይታ ድቻ ጨዋታ እስከ እረፍት ያለምንም ግብ የተጠናቀቀ ቢሆንም በሃዋሳ በጣለው ከባድ ዝናብ ሜዳው ማጫወት እንደማይችል የጨዋታ አመራሮች በማረጋገጣቸው መቋረጡ ይታወቃል። ከዛሬ ሁለቱ ጨዋታዎች ቀደም ብሎ ጨዋታው ከቆመበት ደቂቃ(ሁለተኛው አጋማሽ) በሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም ከቀኑ 7 ሰዓት እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር አመልክቷል። በሌላ በኩል ትናንት በተደረገ የ26ኛ ሳምንት ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ፋሲል ከነማን 2 ለ 1 አሸንፏል።
አካባቢ ጥበቃ
የአፍሪካ ሕብረት የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው
May 30, 2023 48
አዲስ አበባ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ስብሰባ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው ። በሕብረቱ ኮሚሽን የተዘጋጀው ስብሰባ የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓስፊክ የብዝሃ ህይወት አለም አቀፍ ስምምነት፣ የኮፕ-15 የተባበሩት መንግስታት የብዝሀ ሕይወት ስብሰባና 19ኛው በንግድ እንቅስቃሴ ምክንያት እንስሳትና እጽዋት ላይ ጉዳት ላለማድረስ የተደረገ ስምምነት ስብሰባ ውጤቶች ትግበራ ላይ ያተኮረ ነው። የአፍሪካ ሕብረት የዘላቂ አካባቢ ጥበቃና ብሉ ኢኮኖሚ ዳይሬክተር ሀርሰን ኒያምቢ ብዝሃ ሕይወት በአፍሪካ ለቱሪዝም፣ ለመድኃኒት (ፋርማሲዩቲካል) ኢንዱስትሪ እና ንግድ ዘርፍ ያለው ፋይዳ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።   ከብዝሃ ሕይወት የአካባቢን ማህበረሰብ በሚፈለገው መልኩ ተጠቃሚ አለመሆን፣ ሕገ-ወጥ ንግድ እና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮች ናቸው ብለዋል። በመሆኑም በዓለም የብዝሃ ሕይወት ስብሰባ ውጤቶችንና ስምምነቶችን በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል። በብዝሃ ሕይወት ላይ ትኩረት ያደረጉ መርሐ-ግብሮችን፣ የእንስሳትና እጽዋት ሕገ-ወጥ ንግድን ለመከላከል የተዘጋጀውን ስትራቴጂና ቀጣይነት ያለው የደን አስተዳደር ማዕቀፍን መተግበር እንደሚያስፈልግ ነው ዳይሬክተሩ ያመለከቱት።   የአውሮፓ ሕብረት ተወካይ አውሬሊ ጎዴፍሮይ አፍሪካ የብዝሃ ሕይወትና አካባቢ ጥበቃ ድጋፉን እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ለአፍሪካ ቀጣይነት ያለው የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ እና አጠቃቀም ዓለም አቀፍ ትብብርና ጥምረትና የገንዘብ ድጋፍ ወሳኝ እንደሆኑም አመልክተዋል።   የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ አየር ንብረት ለውጥና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዳይሬክተር ጂን ፓል በበኩላቸው አገራት ቀጣይነት ያለው የብዝሃ ሕይወት እንዲኖር እያከናወኑ ያለውን ተግባር ያነሱ ሲሆን ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ተጠቃሽ መሆኑን አንስተዋል። በባለሙያዎች ደረጃ የተጀመረው ስብስባ እስከ ነገ ይቆያል። በሚኒስትሮች ደረጃ የሚደረገው ስብስባ ከነገ በስቲያ የሚጀመር ሲሆን በባለሙያዎች ደረጃ በቀረቡላቸው አጀንዳዎች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በዞኑ ከ180 ሚሊዮን በላይ ችግኝ መትከል የሚያስችል ጉድጓድ መዘጋጀቱ ተገለጸ
May 30, 2023 46
አዳማ ግንቦት 22/2015 (ኢዜአ) በምስራቅ ሸዋ ዞን በአረንጓዴ አሻራ መርሓ ግብር ከ180 ሚሊዮን በላይ ችግኝ መትከል የሚያስችል ጉድጓድ መዘጋጀቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለፀ። በዞኑ አቃቂ ወረዳ ቢልብሎ ቀበሌ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው አምስተኛው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኝ መትከያ ጉድጓድ ዝግጅት ትናንት ተካሂዷል። የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ተሾመ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት በዞኑ ከ260 ሚሊዮን በላይ የተለያዩ ችግኞች መትኪያ ጉድጓድ ለማዘጋጀት ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል።   በእስከ አሁኑ ሂደት 182 ሚሊዮን ጉድጓድ መዘጋጀቱን የገለፁት ሃላፊው ከእቅዱ 70 በመቶ ተሳክቷል ነው ያሉት። በዞኑ 11 ወረዳዎች በሚገኙ 292 ተፋሰሶች ተለይተው ችግኝ መትከያ ጉድጓድ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጡ የቆላ ዛፎች በስፋት ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል። በዚህም ቴምር፣ ቀርከሃ፣ ግሽጣ፣ ዜይቱንና ሌሎች ዛፎች እንዲሁም የእንስሳት መኖ እንደሚገኝበትም ገልጸዋል። በችግኝ ጉድጓድ ዝግጅቱ አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ ሴቶችና ወጣቶች፣ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። 52 የመንግስት የችግኝ ጣቢያዎችን ጨምሮ በ1ሺህ 900 የግለሰቦችና ማህበራት የተለያዩ አገልግሎት የሚሰጡ ከ260 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የምስራቅ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ በበኩላቸው የችግኝ ዝግጅቱ ከሰውና እንስሳት ንኪኪ ነፃ የሆኑና ባለፈው በጋ የእርከን ማሰርና የተፋሰስ ልማት የሰራንባቸው ተራራዎችና የተራቆቱ ቦታዎች ላይ ነው ብለዋል። ዘንድሮ የሚተከሉ ችግኞች እንደ ከዚህን በፊቱ የደን ልማት ብቻ ላይ ትኩረት ያደረጉ ሳይሆን ለምግብነትና ለአፈር ለምነት ጨምር ትልቅ ፋይዳ ያላቸውን ችግኞች በስፋት ለመትከል ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው ብለዋል።   ''የጉድጓድ ዝግጅት እያከናወንበት ያለው የቢልብሎ ተራራ ከአምስት ዓመት በፊት የተራቆተና ምንም አይነት የዛፍና የሳር ዝርያ የሌለበት ነው'' ያሉት አቶ አባቡ ''በአረንጓዴ አሻራ ላይ በሰራ ነው ስራ ዛሬ የምታዩትን ውጤት አግኝተናል'' ነው ያሉት ። በዚህም የተራቆቱ መሬቶች መልሶ አገግመዋል፣ ወንዞችና ዥረቶች መመለስ ከመቻላቸው ባለፈ ከቢልብሎ ተራራ ክረምቱን እየወረደ አርሶ አደሩ የሚቸገርበትን ጎርፍ ማስቀረት እንደተቻለም ገልጸዋል። በአቃቂ ወረዳ የቢልብሎ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት መኮንን ቱፋ በበኩሉ ቢልብሎ ተራራ ምንም አይነት ዛፍና ሳር ያልነበረበት ያገጠጠና የተራቆተ ቦታ ነበር ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በእርከን ማሰር፣ በተፋሰስ ልማትና በአረንጓዴ አሻራ በሰራነው ስራ ተራራው ተመልሶ በደን እየተሸፈነ ከመሆኑም ባለፈ የደረቁ ወንዞችና ዥረቶች ተመልሰው አሁን እየተጠቀሙበት መሆኑን አውስተዋል።
በጋምቤላ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር   ከ11  ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለመትከል  ዝግጅት  እየተደረገ ነው - ቢሮው
May 27, 2023 102
ጋምቤላ ግንቦት 19 /2015 (ኢዜአ)፡- ዘንድሮው በሚካሄደው አምስተኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በጋምቤላ ክልል ከ11 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታወቀ። እየተዘጋጁ ከሚገኙት ውስጥ ከ50 ከመቶ በላይ የሚሆኑት ለሌማት ቱሩፋት ስኬታማነት የሚያግዙ የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን ቢሮው ገልጿል። የቢሮው ኃላፊ አቶ አጃክ ኡቻላ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተራቆቱ አካባቢዎችን ወደ ቀድሞው ይዞታ በመመለስ ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው። ዘንድሮ በሚካሄደው አምስተኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሉ ከ11 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ10 ሚሊዮን በላይ ለተከላ መሰናዳቱን አስታውቀዋል። በክልሉ ዘንድሮ ከሚተከሉት ችግኞች መካከል ከ50 ከመቶ በላይ የሚሆኑት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መሆናቸውን አስረድተዋል። ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ካላቸው ችግኞች መካከል ማንጎ፣ አቡካዶ፣ ብርቱካንና ፓፓያ እንደሚገኙበት ጠቅሰው፤ እነዚህም የሌማት ቱሩፋት መርሃ ግብርን ስኬታማ ለማድረግ የሚያግዙ የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኞቹ በ2 ሺህ 496 ሄክታር በተራቆቱ አካባቢዎችና በቤት ጓሮ አካባቢዎች የሚተከሉ ይሆናል ብለዋል። በክልሉ በአራተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተተከሉት ከ10 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መካከል በተደረገላቸው እንክብካቤ 86 በመቶ መጽደቃቸንውም አቶ አጃክ ገልጸዋል። በጋምቤላ ክልል ባለፉት አራት ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተተከሉ ከ24 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ከ17 ሺህ 980 ሄክታር በላይ የተራቆተ መሬት በደን መሸፈን እንደተቻለ ከክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።  
ሀገር በቀል ዕፅዋትንና እንስሳትን ጨምሮ የብዝኃ ሕይወት መመናመንን ለማስቀረት ማህበረሰቡን ያሳተፈ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃን ማጠናከር ይገባል -ተመራማሪዎች
May 27, 2023 126
አዲስ አበባ ግንቦት 19/2015(ኢዜአ):- ሀገር በቀል ዕፅዋትንና ብርቅዬ እንስሳትን ጨምሮ የብዝኃ ሕይወት መመናመንን ለማስቀረት ማህበረሰቡን ያሳተፈ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃን ማጠናከር እንደሚገባ የዘርፉ ተመራማሪዎች ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብዝኃ ህይዎት ኢንስቲትዩት በበኩሉ የብዝኃ ሕይወት ሀብቶችን ጠብቆ ለማቆየት የመገኛ አካባቢያቸውን የማስጠበቅና ዝርያዎችን በማዕከላት የማንበር ተግባራትን እያከናወንኩ ነው ብሏል። ምሁራኑ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የሰው ልጅ ሕልውና ዋስትና የሆነው ብዝኃ ሕይወት የሕልውና አደጋ ተደቅኖበታል ብለዋል። ለብዝኃ ሕይወት አደጋ ለይ መውደቅና መመናመን የኢንዱስትሪ መስፋፋትን እና የህዝብ ቁጥር መጨመርን እንደ ምክንያትነት አንስተዋል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የብዝኃ ሕይወት ተመራማሪው ፕሮፌሰር ሰብስቤ ደምሰው፤ የአየር ንብረት መዛባት ለብዝኃ ህይወት መመናመን አንዱ መንስኤ መሆኑን ጠቅሰዋል። የብዝኃ ሕይወትን ለመታደግ እንደ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያሉ ማህበረሰቡን የሚያሳትፉና ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጡ ተግባራትን ማጠናከርና ግንዛቤን ማስፋት ይገባል ነው ያሉት። የመሬት ይዞታ አጠቃቀምን ማስተካከልም ሌላኛው ለብዝኃ ህይወት መጠበቅ መፍትሔ መሆኑን አንስተዋል።   በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የብዝኃ ሕይወት ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አየሁ ፈቃዱ እንደሚሉት፤ የህዝብ ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ መምጣቱ ለብዝኃ ህይወት መመናመን መንስኤ መሆኑን ተናግረዋል። አንዳንድ የዕፅዋት ዝርያዎች ለመጥፋት መቃረባቸውን ጠቅሰው፤ይህን ስጋት ለመቀልበስ የብዝኃ ሕይወት ጥበቃ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል። በዚህም አርሶ አደሩ እየተሳተፈባቸው ያሉ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የብዝኃ ሕይወት ማገገም ስራ ሲሰራ ከቦታ መረጣ ጀምሮ ማህበረሰቡን ማወያየትና በባለቤትነት እንዲሳተፍ መንግስት በትኩረት እንዲሰራም አመላክተዋል። በከተማ መስፋፋት፣ በእርሻ መሬት መስፋፋት ምክንያት የመጥፋት አደጋ እየተጋረጠባቸው ያሉት የእንስሳት እና የዕፅዋት ዝርያዎችን ህልውና ለመታደግ፤ በጥናት ላይ የተመሰረተ ልዩ እቅድ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። ለዚህም በምርምር ተቋማት የተካሄዱ ጥናቶችን ወደ ተግባር ማስገባት እንደሚገባ አስረድተዋል።   በጅንካ ግብርና ምርምር ማዕከል ተመራማሪ ምትኩ አየለ በበኩላቸው፤ በተለያዩ ምክንያቶች በደኖች ላይ የሚደርሰው ጉዳት አጠቃላይ ብዝኃ ሕይወት እንዲመናመን እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ይህንን ችግር ለመከላከል በዋናነት ዛፎችን በመትከል እና የአፈር ለምነትን በማሻሻል የደን ሽፋንን ማሳደግ እንደሚገባ ምክረ ሀሳባቸውን ሰጥተዋል።   የኢትዮጵያ ብዝኃ ህይዎት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ፈለቀ ወልደየስ፤ የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ሀብት የሕልውና አደጋ እያጋጠመው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ ሀገር በቀል ዕፅዋትን እና በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ እንስሳትን ጨምሮ የብዝኃ ሕይወት ሀብትን ጠብቆ ለማቆየት የመገኛ አካባቢያቸውን የማስጠበቅና ዝርያዎችን በማዕከላት የማንበር ተግባራትን እያከናወነ ነው ብለዋል።              
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ፕሬዝዳንት ፑቲን ለአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
May 25, 2023 170
አዲስ አበባ ግንቦት 17/2015 (ኢዜአ)፦የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን ለቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለአሁኑ የአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንከዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት ለአፍሪካውያን የድል ምልክት ነው ያሉ ሲሆን የአፍሪካውያን የነጻነት፣የሰላምና የብልጽግና ፍላጎት ማሳያ ነው ብለዋል። ህብረቱ ከተመሰረተበት ግዜ አንስቶ ለብዙ አስርተ ዓመታት በዓለም አቀፍ መድረኮች አፍሪካውያንን በመወከል የባለብዙ ወገን ውይይቶችንና ትብብርን በማጎልበት ትልቅ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት ለችግሮቻቸው በጋራ ምላሽ የሚሰጡበትን መንግድ ያመቻቸ መሆኑን ጠቁመው አህጉራዊ ትብብርን በተለያዩ መስኮች እንዲያጠናከሩም መንገድ ከፍቷል ብለዋል። በዚህም ለአፍሪካ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት የላቀ ሚና ማበርከቱንና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ያላትን ተሳትፎ እንድታሳድግ ህብረቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ሩሲያ ከአፍሪካ አጋሮቿ ጋር ያላትን ወዳጅነት ለማጠናከር ልዩ ትኩረት ትሰጣለች ያሉት ፕሬዝዳንቱ እ.አ.አ በ2019 የተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ -ሩሲያ ጉባኤ በአፍሪካና በሩሲያ መካከል ያሉ ትብብሮች እንዲጠናከሩ አስችሏል ብለዋል። በመጪው ሃምሌ ወር በሩሲያ የሚካሄደው ሁለተኛ የአፍሪካ ሩሲያ ጉባኤም ሩሲያ ከአፍሪካ ጋር ለሚኖራት ትብብር አዲስ ምዕራፍ እንደሚፈጥር ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 3167
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተገለጸ
Dec 20, 2022 1626
አዲስ አበባ ታኅሳስ 11/2015 (ኢዜአ) አህጉራዊው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና አፍሪካ ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ግንኙነትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተመላከተ። የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ከአፍሪካ ጋር ያላት የንግድ ትስስር ከባህረ-ሰላጤው ሃገራት መካከል በቀዳሚነት እንደሚጠቀስም ተገልጿል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዊሊያም ስቴንሀውስ ከሲ ጂ ቲ ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በተለይም ዱባይ የአፍሪካን ንግድና ኢንቨስትመንት በተመለከተ ዋና ማዕከል ሆናለች ብለዋል። በዱባይ 25ሺህ ገደማ የአፍሪካ ካምፓኒዎች እንደሚንቀሳቀሱ አመልክተው ይህም ሀገሪቱ በነጻ የንግድ ቀጣናው የቢዝነስ አጋር እንድትሆን አስችሏታል ነው ያሉት። አፍሪካውያን ባለሃብቶች የግብይት ማዕከላቸውን በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በማድረግና ምርቶችን ወደ አህጉሪቷ በማስገባት በነጻ ንግድ ቀጣናው ስር የገልፍ ሀገራትን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደጉት እንደሚገኝም አስገንዝበዋል። የዱባይ ወደብ በአፍሪካ ያለው ተደራሽነት መስፋፋትም አፍሪካ ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ጋር የሚኖራትን የሎጀስቲክስ አቅርቦት እንደሚያሳድግ በመረጃው ተመላክቷል። ከገልፍ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት ከኢኮኖሚያዊ ትስስር ባለፈ ዲፕሎማሲያዊና ወንድማማችነትን መሠረት ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤሜሬት የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ ናቸው። አምባሳደሩ እንደሚሉት ከመካከለኛው ምስራቅ መነሻቸውን ያደረጉ ባለሃብቶችና የቢዝነስ ሰዎች ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጋር በልዩ ልዩ ዘርፎች ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ይገኛል። እ.አ.አ በጥር 2021 ተግባራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ከአጀንዳ 2063 ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የአህጉሪቱን ወሳኝ የኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም የዲጂታል ንግድ፣ የኢንቨስትመንት ትስስርና ሌሎች የንግድ ግንኙነቶችን በነጻ የንግድ ቀጣና ለማከናውን የተካሄደ ስምምነት ነው።
ሐተታዎች
አፋጣኝ መፍትሔ የሚያሻው የምርታማነት ፀር
May 27, 2023 97
  (ኤልያስ ጅብሪል) አሲዳማ አፈር የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከሰባት በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al+3) ንጥረ- ነገሮች የሚበዙበት አፈር ማለት ነው፡፡ የአፈር አሲዳማነት በሀገራችን በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ የሚገኝ የአፈር ለምነት ችግር ሲሆን፤ ከፍተኛ ዝናብ የሚያገኙና በምርታማነታቸው የተሻሉ ናቸው የሚባሉትን የሀገሪቱን አካባቢዎች ጭምር እየጎዳ መሆኑንም ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት፡፡ የአፈር ጤንነት ችግሮች በሦስት ዋና ዋና መንገዶች ይገለፃሉ፡፡ ይኸውም አሲዳማነት፣ የጨዋማነት ችግር የሚነሳበትና ኮትቻማ/ጥቁር ወይም መረሬ አፈር/ ብሎ ማስቀመጥ እንደሚቻል በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊ ፋኖሴ መኮንን ይናገራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ከ15 ሚሊየን ሄክታር በላይ የሚታረስ መሬት ሲኖር ወደ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በአሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነ ነው የጠቀሱት፡፡ አፈር ሰብሎች የሚፈልጓቸውን ንጥረ-ነገሮች በተሟላና በተመጣጠነ መልኩ ሳይዝ ሲቀር ምርታማነት ጥያቄ ውስጥ እንደሚወድቅ አቶ ፋኖሴ ይገልጻሉ። ከዚህ አኳያ በኢትዮጵያ ከ1 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጎዳ በመሆኑ ምርታማነቱ ምንም በሚባል ደረጃ የሚቀመጥ መሆኑን ይጠቁማሉ። እፅዋት ከአየር፣ ውሃና የፀሐይ ብርሃን በተጨማሪ 18 ዓይነት ንጥረ-ነገሮችን ከአፈር ውስጥ ሊያገኙ እንደሚችሉ ነው ኃላፊው የገለጹት፡፡ የአፈር አሲዳማነት መንስኤዎች አሲዳማነት በአንድ ጊዜ ተፈጥሮ የሚቆይ ሳይሆን በሂደት እየጨመረ እና እየተስፋፋ የሚሄድ ክስተት ነው፡፡ ለአፈር አሲዳማነት በዋነኝነት የዝናብ መብዛት፣ የአፈር መሸርሸር፣ የሰብል ተረፈ-ምርት ሙሉ በሙሉ ከማሳ ማንሳት እና ፍግ አለመጠቀም፣ እንዲሁም አሲዳማ ዝናብ የመሳሰሉት አፈር ውስጥ ያሉ ለተክሉ እድገት ጠቃሚ ንጥረ-ነገሮች እንዲሟጠጡ እንደሚያደርግ በመንስኤነት ይጠቀሳሉ። የአፈር አሲዳማነት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚስተዋል ሲሆን ለአብነትም አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ተጠቃሾች እንደሆኑ አቶ ፋኖሴ ተናግረዋል፡፡ አሲዳማ አፈርን በኖራ የማከም ዘዴ አሲዳማ አፈርን ለመከላከል በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ መንገዶች ከሚወሰዱ እርምጃዎች ባሻገር አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ በዋናነት የሚጠቀስ መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ አፅንዖት ሰጥተው የተናገሩት፡፡ የተለያዩ አፈርን የማከሚያ ግብአቶች ያሉ ቢሆንም በቀላሉ ከመገኘትና ከዋጋው ርካሽነት አንፃር ካልሽየም ካርቦኔት ወይም “ የግብርና ኖራ" እየተባለ የሚጠራው በስፋት አገልግሎት ላይ እንደሚውል ገልጸዋል፡፡ ወደ 15 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር የሚታረስ መሬት ሲኖር፤ ከዚህ ውስጥ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር ወይም ከ43 በመቶ የማያንሰው በአሲዳማ አፈር የተጠቃ መሆኑን ጠቅሰው፤ ወደ 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነው በጠንካራ አሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነና በኖራ መታከም ያለበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ጠንካራ አሲዳማ አፈር ስንል የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከ 5 ነጥብ 5 በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al3+) ካታየኖች የሚበዙበት አፈር ሲሆን፤ የእነዚህ ካታየኖች መብዛት የሰብሎችን ሥር በመመረዝ በዕድገታቸው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን እንደሚፈጥር ነው ከግብርና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ የሚጠቁመው፡፡ ፒ ኤች መጠኑ ከሰባት ወደ ዜሮ እየቀነሰ ሲሄድ የአሲድነቱ ጥንካሬ የሚጨምር ሲሆን ከሰባት ወደ 14 ሲጨምር የጨዋማነቱ ባህሪ እንደሚጨምር ነው የዘርፉ ባለሙያዎች የሚያስቀምጡት። በአገራችን ሁኔታ አሲዳማ አፈርን ለማከም ኖራ መጠቀም የሚያስፈልገው የአፈሩ ፒ ኤች መጠን ከ5 ነጥብ 5 በታች ሲሆን ነዉ፡፡ ኖራ በተፈጥሮ የሚገኝ የካልሲየም እና የማግኒዚየም ካርቦኔት ሃይድሮኦክሳይድ ውህድ ሲሆን፤ አሲዳማ አፈር ውስጥ በሚጨመርበት ወቅት አሲዳማ አፈር ውስጥ የሚገኙትን አልሙኒየም እና ሃይድሮጂን አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን በመግታት የአፈሩን ፒ ኤች መጠን ከፍ በማድረግ ለእፅዋት እድገት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ በአማካይ በአፈር አሲዳማነት የተጎዳ መሬትን ለማከም በሄክታር 30 ኩንታል የግብርና ኖራ እንደሚያስፈልግ ባለሙያዎች ይመክራሉ። በአሲዳማነት የተጠቃ መሬት አሲዳማነትን የሚቋቋሙ ሰብሎች ካልተዘሩበት ወይም አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ ካልተሰራ የሚሰጠውን የአፈር ማዳበሪያ ከጥቅም ውጭ በማድረግ ለኪሳራ ይዳርገናል ነው ያሉት፡፡ እንደ አኩሪ አተር፣ ካሳቫ፣ አናናስ፣ ዳጉሳ፣ ቡና፣ ሻይ እንዲሁም የስንዴ ዝርያዎች አሲድን የመቋቋም ባህሪ እንዳላቸውም ተመላክቷል፡፡ ግብርና ሚኒስቴር በአሲዳማነት ከተጠቃው 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነውን በአሥር ዓመት ውስጥ ለማከም ዕቅድ የያዘ ቢሆንም በዕቅዱ መሰረት በዓመት 400 ሺህ ሄክታር መሬት ለማከም ወደ 5 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት፡፡ ከበጀት አንጻር ይህን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በየዓመቱ ከመንግሥት ካዝና ማግኘት ከባድ በመሆኑ ከእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች፣ ከአጋር አካላት ድጋፍ ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን ነው ያስታወቁት። ምንም እንኳን በአሲዳማነት የተጠቃውን አፈር ማከም ወጪው ከፍተኛ ቢሆንም አፈሩ ሳይታከም በቆየ ቁጥር ከምርት ውጭ የመሆን ዕድሉ እየጨመረ ስለሚሄድ አገርን የሚያሳጣው ዋጋ ከፍተኛ እንደሚሆን በውል መረዳት ያሻል። በዚህም የአፈር አሲዳማነት ጉዳይ መፍትሔ ካልተሰጠው ምርታማነትን ከ50 በመቶ እስከ 100 በመቶ ሊያሳጣ እንደሚችል ነው በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊው ፋኖሴ መኮንን የሚናገሩት፡፡ ከአፈር አሲዳማነት የተነሳ በየዓመቱ ወደ 9 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በኢትዮጵያ ደረጃ በስንዴ ከሚሸፈነው መሬት ብቻ እየታጣ እንደሆነ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ይህ በስንዴ ብቻ ከሚሸፈን መሬት የተወሰደ ግምት ሲሆን በገብስ፣ ጤፍ ወዘተ… ቢታሰብ ምን ያህል የምርት ማሽቆልቆል እንደሚያስከትል ማወቅ ይቻላል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ የስንዴ ምርት በአማካይ በሄክታር እስከ 40 ኩንታል ምርት ሊሰጥ ይችላል፤ ሆኖም ግን የአፈር ጤንነቱን በመጠበቅ አስፈላጊውን ግብአት የምንጠቀም ከሆነ በሄክታር 60 ኩንታል በማምረት አገራችን የጀመረችውን ምርትና ምርታማነትን የማረጋገጥ ሥራ ማከናወን ያስችለናል ነው ያሉት፡፡ ይህንንም ከግብ ለማድረስ የግብርና ሚኒስቴር የመጀመሪያው የትኩረት አቅጣጫው የአሲዳማ አፈር ልማት መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ ያስረዱት፡፡ አሲዳማ አፈሩን ለመከላከል በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ባለፉት ሦስት ዓመታት 38ሺህ 369 ሄክታር መሬት በኖራ የማከም ሥራ መከናወኑ ተገልጿል። ይህ ከሚኒስቴሩ ዕቅድ አኳያ ሲታይ በጣም ዝቅተኛ አፈጻጸም ነው። የአፈር አሲዳማነትን ለማከም የግብርና ኖራ ምርት ላይ የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች አቅርቦቱን በሚፈለገው ደረጃ ቢያቀርቡም፤ የኖራ ምርቱ በብዛት ያለበት ቦታ እና አሲዳማ መሬቱ የሚገኝበት ርቀት በተቃራኒው በመሆኑ ከትራንስፖርት አንጻር ያለው ችግር ሥራውን አድካሚ እንዳደረገው ነው የሚኒስቴሩ መረጃ የሚያመለክተው። ነገር ግን አርሶ አደሩ አንድ ጊዜ መሬቱን በኖራ ማከም ከቻለ እስከ አምስት ዓመት ሊያገለግለው ይችላል። ከዚያም በኃላ ቢሆን የተወሰነ የምርት መቀነስ እንጂ በምርታማነት ላይ የጎላ ችግር አይኖረውም ነው ያሉት። ስለሆነም ኖራን የመጠቀም ሁኔታ አቅም ያለው አርሶ አደር በግዥ መልክ እንዲጠቀም፤ አቅም የሌለው ደግሞ መንግሥት ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል። እንደ ምዕራብ ኦሮሚያ ነጁ፣ መንዲ፣ ምዕራብ ወለጋ እንዲሁም በአማራ ክልል አዊ ዞን፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አብዛኛውን ወረዳዎች በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጠቁ በመሆናቸው ምርት ለመስጠት የማይችሉበት ደረጃ ላይ እየደረሱ መሆኑን አቶ ፋኖሴ ገልጸዋል። ዝዋይ፣ ሐዋሳ፣ መራቤቴ፣ ደጀን፣ ጉደርና የመሳሰሉት በመንግሥትም ሆነ በግል የግብርና ኖራ ምርት የሚቀርብባቸው ቦታዎች መሆናቸው ነው የተጠቆመው። በእነዚህ ቦታዎች የምርትና የጥሬ ዕቃ ችግር የሌለና የግብርና ኖራ ዋጋም በኩንታል እስከ 350 ብር እየተሸጠ ነው ብለዋል። የአፈር አሲዳማነት በረዥም ጊዜ የተፈጥሮ መዛባት ሂደት ውስጥ የሚከሰት እንደመሆኑ መጠን አንዴ ችግሩ ከተከሰተ በኋላ መፍትሔ በመስጠት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ወጪ እና ርብርብ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም ችግሩ ከመከሰቱ በፊት የአፈር አሲዳማነትን ለመከላከል የሚያስችሉ እርምጃዎችን መውሰድ ተገቢነት ያለው ጉዳይ እንደሆነ ነው የተጠቆመው፡፡ መንግሥት በያዘው የሌማት ትሩፋትና የግብርና ኢኮኖሚ አቅጣጫ በተለይም የስንዴ ምርት ከራስ ፍጆታ አልፎ ለሌሎች አገራት ምርቱን በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት በሚደረገው ጥረት የአፈር ምርታማነትን/ጤንነቱን መጠበቅ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑ የግድ ነው። “ለም አፈር በሌለበት ምርትና ምርታማነት የማይታሰብ ነው” የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ ግብርና የመሪነት ተግባሩን እንዲወጣ በቅድሚያ የአፈር ጤንነት ሊጠበቅ ይገባል ብለዋል። በመሆኑም ከዚህ በፊት ያለውን የግንዛቤ ችግርና ከአመራሩ እስከ አርሶ አደሩ ያለውን ክፍተት በመቅረፍ ችግሩን ለመቀነስ እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል። ሁሉንም ነገር ከመንግሥት መጠበቅ የለብንም የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ በቅድመ-መከላከል ሥራ ችግኝ በመትከል፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ በማከናወን፣ በተፈጥሮ ማዳበሪያ (ኮምፖስት) የራስን ማሳ በመንከባከብ፣ አማራጭ ሰብሎችን እያፈራረቁ በመዝራት፣ አሲዳማነትን መቋቋም የሚችሉ ተክሎችን በመምረጥ ማልማት እንዲሁም የግብርና ኖራ በመጠቀም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አብራርተዋል። በሀገራችን በተለያዩ የምርምር ተቋማት የተሰሩ ምርምሮች እንደሚያሳዩት አሲዳማ አፈርን ለማከም የተፈጥሮ ማዳበሪያዎችን ከኖራ ጋር አቀናጅቶ በመጠቀም በዋና ዋና ሰብሎች ላይ እስከ ሁለት እጥፍ የምርት ጭማሪ ማግኘት እንደሚቻል ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በመሆኑም አርሶ አደሮች ኖራ በግዥና በብድር የሚያገኙበትን ሥርዓት በተጠናከረ አግባብ መተግበር ያስፈልጋል። ልክ እንደ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በግዥ ወይም በብድር የግብርና ኖራ በማቅረብና በአሲዳማነት የተጎዳው መሬት እንዲያገግም ማድረግ ላይ አትኩሮ መስራት ሌላው የመፍትሄ አካል ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል። የእርሻ መሬት አያያዝና እንክብካቤ ጉዳይ የህግ ማዕቀፍ ኖሮት በዚያ አግባብ ተግባራዊ ማድረግም በተለይ በአሲዳማነት የመጠቃት አዝማሚያ የተጋረጠበትን የእርሻ መሬት ለመታደግና የተጎዳውንም እንዲያገግም ለማከም የሚሰሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ያስፈልገዋል። ከዚህ ባለፈም በአንድ የእርሻ ቦታ ላይ የተለያዩ ሰብሎችን መዝራት፣ አፈር ውስጥ ህይወት ያላቸው ነገሮች እንዲኖሩ ማድረግና የአፈሩን እርጥበታማነት ማዝለቅ ተገቢ ይሆናል።            
አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታና አብሮነት
May 3, 2023 873
በጣፋጩ ሰለሞን አገራችን ኢትዮጵያ የተለያየ ቋንቋ፣ ባህልና እምነት ያላቸው በርካታ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ተቻችለው፣ ተከባብረው፣ ተዋደው፣ በአንድነትና በአብሮነት በፍቅር የሚኖርባት አገር ነች። በዚህም የብሄር ብሄረሰቦች ሙዝዬም ነች የሚል አድናቆትን ተጎናፅፋለች-ኢትዮጵያ። እነዚህ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች የራሰቸው መገለጫ የሆኑ ቱባ ባህል አላቸው። ኢትዮጵያውያን ለዘመኑ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጥበብ መሰረት የሆኑ የአያሌ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤቶች ናቸው። ባህላዊ የመድኃኒት ቅመማና የህክምና ጥበብ ኢትዮጵያ ለዓለም ካበረከተቻቸው ትሩፋቶች መካከል አገር በቀል ዕውቀቶች ተጠቃሽ እንደሆኑ የታሪክ ድርሳናትና ሌሎች የየዘርፉ ተጓዳኝ መረጃዎች ያስረዳሉ። በተለይ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የተጠቀሙባቸውና እየተጠቀሙባቸው ያሉ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሌሎችም ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀሱ ናቸው። በጂንካ ዩኒቨርስቲ 5ኛው አገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ ሰሞኑን ተካሂዷል። በኮንፈረንሱ በአገር በቀል ግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም፣ለአብሮነት ትስስር እና ለአገራዊ ዕድገት ያላቸው ሚና የሚል እሳቤን ዓላማ ያደረገ ጥናት ቀርቧል። ጥናቱ እ.ኤ.አ ከ2018 እስከ 2022 ባሉ ዓመታት በመስቃን እና በማረቆ ህዝቦች ባህላዊ የግጭት አፈታት ላይ መሰረት አድርጎ የተካሄደ ነው። ጥናቱን ያካሄዱት "አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሰላም፣ ለፀጥታ እና ለዕድገት ያላቸው አስተዋፅኦ፤The Role of Indigenous conflict resolution Mechanism for peace,Security ,and Sustainable Development in Ethiopia " በሚል ርዕስ ያካሄዱት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ ዮሐንስ ተስፋዬ ናቸው። የጥናቱ ግኝት እንደሚያመለክተው ዘመናትን ተሻግረው እዚህ የደረሱ የሰላም ግንባታና ማጠናከሪያ የሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች አሁን ለደረስንበት ሳይንሳዊ ጥበብ መጎልበት እያገለገሉ ነው። የጥናት አቅራቢው ለኮንፈረንሱ ታዳሚዎች እንዳብራሩት ጥናቱ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ለአብሮነትና ለዕድገት አይተኬ ሚና አላቸው። እነዚህን አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች በአግባቡ መጠቀም ይገባል። እሳቸው እንዳብራሩት በአገራችን ሶስት አይነት የግጭት አፈታት ዘዴዎችን እንጠቀማለን። የወንጀልና የፍትሐብሔር ህጎች፣ እንደ ሽምግልና ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች እና ከሃይማኖታዊው ደግሞ ሸርዓ ከምንጠቀምባቸው የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ናቸው። ተመራማሪ ዮሐንስ እንዳሉት ጥናቱ በተካሄደበት በጉራጌ ዞን በመስቃን እና በማረቆ መካከል አጋጥሞ የነበረውን አለመግባባት ከመፍታት አኳያ ከዘመናዊ እውቀቶች ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ትልቅ ሚና ነበራቸው። በመስቃን እና በማረቆ ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት ከመስቃን፤ ከማረቆ እንዲሁም ከአጎራባች የኦሮሚያና ስልጤ ዞኖች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ተሳትፈዋል። በመስቃን እና በማረቆ መካከል ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት የተሳተፉት የሀይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች ግጭቱን ለመፍታት የተጠቀሙት ጥበብ አገር በቀል ዕውቀቶች በዘመናዊ ህግና አሰራር የማይቻሉትን የመፈጸምና ማህበራዊ አንድነትን ከማጠናከር አንፃር ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የጥናቱ ግኝት አመላክቷል። አለመግባባቱን ለመፍታት 26 ዙር ለመሸምገል ተቀምጠዋል። በማሸማገሉ ሂደት የተሳተፉት የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሁለቱን ማህበረሰቦች ለማቀራረብና በአካባቢው እረቀ-ሰላም ለማወርድ የከፈሉት መስዋዕትነት ቀላል አለመሆኑን በአጽኖኦት አስረድተዋል። የትኛውንም ውጣ ውረድና ጫና ተቋቁመው ሳይታክቱ ችግሩን የፈቱበት መንገድ ለዘመናዊው አስተዳደር ትምህርት የሚሰጥና በቅርስነት ለትውልድ የሚተላለፍ ሰናይ ተግባር መሆኑንም አስረድተዋል። ግጭቶች ቀደም ሲል የነበሩ፣ አሁንም ያሉና ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው። በተለያዩ ምክንያቶች የሚያጋጥሙ ግጭቶችን ፖለቲካዊ ትርጉም በመስጠት ከማጦዝ ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ተጠቅሞ ለማርገብ መስራት አዋጭና ተመራጭ መንገድ መሆኑን የጥናቱን ግኝት ዋቢ አድርገው ተመራማሪ ዮሐንስ መክረዋል። ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ለአገር በቀል እውቀቶች ተገቢውን ዕውቅና መስጠት ይገባል። አገር በቀል ዕውቀቶችን በትምህርት ሥርዓት ውስጥ አካቶ ለማጎልበት የተጀመረው አበረታች ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል። አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ አብሮነትን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው ያሉት ደግሞ የጂንካ ዩኒቨርስቲ የባህል ተመራማሪና የዩኒቨርስቲው የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ኤሊያስ ዓለሙ ናቸው። አክለውም ዘመናዊ ሕግን ተከትሎ በሚሰጡ ብያኔዎች አንዱ ወገን የሚደሰትበት ሌላኛው ደግሞ ቅር ተሰኝቶ የሚከፋበት ናቸው ይላሉ። በማህበራዊ ሸንጎ ግን ሁለቱም ወገን የሚደሰቱበት፣ ከልብ ይቅር ተባብለው ችግሮቻቸውን የሚፈቱበትና ዘላቂ እርቀ-ሰላም የሚያወርዱበት እንደሆነም ያስረዳሉ። ዶክተር ኤሊያስ አክለውም ይህም ማህበራዊ አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው የላቀ ነው። የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን ለመፍታትና በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በአገራችን ቱባ ባህሎች ውስጥ ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን መጠቀም ይገባል። በባህላዊ እሴቶቻችን ውስጥ ያሉ አገር በቀል ዕውቀቶች ቀጣይነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ እንዲውሉና ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆኑ ዕውቅና መስጠት፣ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ማካተት፣ በአግባቡ አደራጅቶና ሰንዶ ለትውልድ ማስቀመጥ እንደሚገባ አመላክተዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራን የሚጠበቅብንን ኃላፊነት በአግባቡ ልንወጣ ይገባል ይላሉ። አቶ መምህሩ ገዙሜ በጂንካ ዩኒቨርስቲ በሶሻል አንትሮፖሎጂ የትምህርት ክፍል የሶሽዮሎጂ መምህር ናቸው። አገር በቀል ዕውቀቶች ለአገራዊ ችግሮቻችን መፍቻ መንገዶች ናቸው ይላሉ። የሳይንሳዊ ምርምሮች ፅንሰ-ሀሳብ መነሻው አገር በቀል ዕውቀቶች እንደሆኑ ይጠቅሳሉ። በአገራችን በርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ቢኖሩም እንዳለመታደል በአግባቡ መጠቀም አልቻልንም ሲሉም ያክላሉ። እሳቸው እንዳሉት መንግሥት አሁን ለአገር በቀል ዕውቀቶች የሰጠው ዕውቅና ለአገር በቀል ዕውቀቶች መጎልበትና ጥቅም ላይ መዋል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ይህን ዕድል በመጠቀም አገር በቀል እውቀቶች ጎልተው እንዲወጡና በትምህርት ሥርዓቱ ተካተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት ይገባል። በተለይ የማህበረሰቡ የግጭት አፈታት ዘዴና በምክክር ችግሮችን የመፍታት ጥበብ የታሰበው አገራዊ የምክክር መድረክ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። በመሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ፣ ለኢትዮጵያውያን የአብሮነት ትስስርና መስተጋብር መጠንከር እንዲሁም ለአገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና እጅግ የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ተገንዝቦ ተገቢውን ዕውቅና በመስጠት መጠቀም ይገባል።
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ
Apr 2, 2023 1372
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ በሰለሞን ተሰራ በታሪክ ተመዝግበው የምናገኛቸው አያሌ መልካምና በጎ ነገሮች የመኖራቸውን ያህል በተቃራኒው ደግሞ የሰው ልጆች ግፍና በደል ሲፈጽሙና ሲያስተናግዱ ኖረዋል። በዚህም በተለይ በበደሉ ገፈት ቀማሾች ላይ የሚደርሰው ድንጋጤ፣ ሰቆቃና ሀዘን ሰዎችን ለበቀል እያነሳሳ ሌላ ጥፋት ሲያስከትል ማስተዋልም እንግዳ ነገር አይደለም። በዚያው ልክ ሰዎች የደረሰባቸውን ግፍና መከራ ለማራገፍ ፍትህን ሲሹና ሲጠይቁ ይስተዋላል። እምባቸው የሚታበሰው፣ ቁስላቸው የሚሽረው ለደረሰባቸው በደል ካሳ የሚሆን ፍትህ ሲያገኙ ብቻ እንደሆነም ያምናሉ። በርካታ አገራትም በታሪክ ውስጥ ላጋጠሟቸው ስብራቶች የሽግግር ፍትህን አማራጭ አድርገው በመጠቀም ለችግሮቻቸው መፍትሄ ያበጃሉ። እኤአ በ1970 ዎቹ መጀመሪያ በምስራቅ አውሮፓ እና ደቡብ አሜሪካ ተግባራዊ በተደረገው የሽግግር ፍትህ በጦርነትና በግፍ አገዛዝ የተበደሉ አካላት ፍትህ እንዲያገኙ የተደረገበት መንገድ ተጠቃሽ ነው። ከዚህ ጊዜ በኋላ የሽግግር ፍትህ በተለይ በመደበኛ የህግ ስርአት ብቻ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስቸግሩ ጉዳዮችን ጭምር በተጠያቂነት፣ በይቅርታ፣ በካሳ ወዘተ መፍትሄ በመስጠት የፍትህ ማስፈኛ መንገድ ተደርጎ ተወስዷል። የሽግግር ፍትህ ማለት በማህበረሰቡ ውስጥ በስፋት ለተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ምላሽ የሚሰጥበት አካሄድ መሆኑን ምሁራን ያስረዳሉ። ይህንን ሂደት ሰላማዊ፣ አካታችና ተደራሽ ለማድረግ የሁሉም ጥረትና አጋርነት ቀዳሚ መነሻ ሊሆን እንደሚገባውም ይገልጻሉ። የሽግግር ፍትህ በአንድ ጊዜ የሚያልቅ ሳይሆን ጊዜ የሚጠይቅና ዓመታትን ሊወስድ የሚችል ነው። ይህም ለተበዳዮች ፍትህ በመስጠት፣ ካሳ በመክፈል፣ የወደሙ ንብረቶችን መልሶ በመገንባትና በመሰል ሂደቶች ሊፈጸም ይችላል። የሽግግር ፍትህ ሀገራት ከብጥብጥ፣ ከፀብና ጥላቻ አዙሪት እንዲወጡ በማድረግ በኩል የማይተካ ሚና እንዳለው የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮዎች ያሳዩናል። በ2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ የፀደቀው የአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ማዕቀፍ፣ የሽግግር ፍትህ ሀገራት የተለያዩ መደበኛ እና ባህላዊ ወይም መደበኛ ያልሆኑ የፖሊሲ እርምጃዎችንና ተቋማዊ አሠራሮችን በመጠቀም የተፈጸሙ ጥሰቶችን፣ ክፍፍሎችንና አለመመጣጠኖችን ለማስወገድና ለደኅንነትም ሆነ ለዴሞክራሲያዊና ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሥርዓት ግንባታ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የሚደረግ ጠቃሚ እና አስፈላጊ ሂደት እንደሆነ ይገልጻል። የሽግግር ፍትህ በግጭት፣ በጦርነት ወይም ጨቋኝ ሥርዓት በነበረበት ወቅት ለተፈፀመ ጥቃት፣ መጠነ-ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና በደል የተሟላ መፍትሄ መስጠት መቻል ነው። ይህም በዋናነት ሙሉ ፍትህ የሚሰጥበትን መንገድ በመዘርጋት ዘላቂ ሰላም፣ እርቅ፣ መረጋጋት እና የህግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት መገንባት የሚቻልበትን ሁኔታ የሚመለከት ነው። በኢትዮጵያ ተግባራዊ ሊደረግ የታሰበውና በፖሊሲ አማራጭ ዝግጅት ሂደት ላይ የሚገኘው የሽግግር ፍትሕ በአራት ዋና ዋና ምክንያቶች አስፈላጊ መሆኑን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል። አንደኛው ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሀገራዊ አውድ ሲሆን በዚህም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ አለመረጋጋት፣ ግጭትና የእርስ በርስ ጦርነት ተከስቷል። ይህም ዜጎችን ለሞት፣ ለአካል ጉዳት፣ ለመፈናቀል ያጋለጠ መሆኑ በገፊ ምክንያትነት ይጠቀሳል። ለነዚህ ችግሮች ከዚህ በፊት የተሰጡ ምላሾች ሙሉ አለመሆናቸው የአጥፊዎችና የተጎጂዎችን ቁጥር ማብዛቱ፣ የበደሎች መደራረብ እና የጥፋቶች ማህበረሰባዊ ቅርጽ መያዝ በመደበኛው የፍትሕ ሥርዓት እና አካሄድ ፍትሕ መስጠትንም ሆነ ይቅርታ እና እርቅን ማከናወን አላስችል ማለቱ የሽግግር ፍትህ ትኩረት እንዲሰጠው አድርጓል። ሁለተኛው የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ማለትም ባለፉ በደሎች ይቅር ለመባባል፣ እርቅ ለማውረድ፣ ሕዝብ ለማቀራረብ፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እና ለተፈጸመ በደል እውቅና ለመስጠት አስፈላጊ በመሆኑ ነው። ሶስተኛው ምክንያት የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ሂደት ሳይተገበር የዴሞክራሲ ሽግግርም ሆነ ዘላቂ ሰላም ማስፈን አይቻልም የሚል ነው። የመጨረሻው በገፊ ምክንያትነት የሚጠቀሰው ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እና የሕግ የበላይነትን ለማስፈን የሽግግር ፍትህ ወሳኝ በመሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በነዚህ ምክንያቶች የሽግግር ፍትሕን ለማስፈን እየሰራች መሆኑ በበርካቶች ዘንድ በአዎንታዊ መልክ ይጠቀሳል። በተለይ የሽግግር ፍትህን ተግባራዊ ካደረጉ አገራት ተሞክሮ በመውሰድ ለውጤታማነቱ ከተሰራ በርግጥም አይነተኛ መፍትሄ ነው። ከአፍሪካ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ በቅርቡ ደግሞ ጋምቢያ የሽግግር ፍትህን ለችግሮቻቸው መፍቻነት ከተጠቀሙ አገራት መካከል ናቸው። ሩዋንዳ ሩዋንዳ እኤአ በ1994 በመቶ ቀናት ብቻ ከነበሯት 7 ሚሊዮን ዜጎቿ 800 ሺዎቹን በግፍ ተነጥቃለች። 2 ሚሊዮን የሚጠጉት በስደት ሀገራቸውን ለቀው ሲወጡ በዚህ የጭካኔ ተግባር ተሳትፎ ነበራቸው የተባሉ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ላይ ክስ በመመስረት ፍትህ ፊት አቅርባቸዋለች። በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት በሀገር ውስጥ ችሎትና በባህላዊ መንገድ በተዳኙት ወንጀለኞች ላይ የተሰጡት የፍትህ ውሳኔዎች አሁን ላይ ሀገሪቱን በዲሞክራሲና በሰላም እንዲሁም በብልፅግና መንገድ መራመድ እንድትችል አድርጓታል። ሩዋንዳውያን በቆየ ሀገራዊ ብሂላቸው ”ሁላችንም የአንድ አባትና እናት ልጆች ነን ይላሉ”። ይህንኑ ብሂል መመሪያቸው በማድረግ በሀገሪቱ ያሉት “ቱትሲ” እና “ሁቱ” የተባሉት ዋነኛ ብሄሮች በአብሮነት ለዘመናት ኖረዋል። ሩዋንዳ በጀርመን የቅኝ አገዛዝ ስር እንደወደቀች የዘር ልዩነቱን ወደፊት ያመጡት ቅኝ ገዥዎች ሁለቱን ብሄሮች የሚያጋጩ ሴራዎችን በመጎንጎን ቱትሲዎችን መግደል የፖለቲካቸው ስልት ማስፈጸሚያ አደረጉት። ይህ ከፋፋይ የፖለቲካ ሴራ በቤልጂየም የእጅ አዙር አገዛዝ ዘመንም እንደቀጠለ ይነገራል። በዚህም ማንነትን መሰረት ያደረገ የፖለቲካ አደረጃጃት፣ የመታወቂያ ወረቀት፣ ቱቲስዎችን በስልጣን ወደፊት ማምጣትና ሁቱዎችን አሳንሶ መመልከትን ባህል አደረጉት። በዚሁ መርዘኛ ሀሳብ መነሻነት ከነጻነት በኋላ እኤአ ከ1959 እስከ 1967 አካባቢ በመንግስት በተደገፈ የዘር ማጥፋት 20ሺ የሚጠጉ ቱትሲዎች ሲገደሉ 300ሺ የሚጠጉ ሀገራቸውን ለቀው ተሰደዱ። በዚህም እኤአ በ1987 በቱትሲዎችና ለዘብተኛ ሁቱዎች የተቋቋመው የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር እኤአ በ1993 የመንግስትን ስልጣን ለመጋራት በቃ። ነገር ግን እኤአ በሚያዚያ 6 ቀን 1994 የሀገሪቱ መሪ የነበሩት ሃባይሪማና በቅጥረኞች በመገደላቸው በሀገሪቱ አመጽ እንዲቀጣጠል ምክንያት ሆነ። ይህን ተከትሎ “ኢንተርሀሞይ” በመባል የሚጠራው የሚሊሽያ ቡድን በቱትሲዎችና በለዘብተኛ ሁቱዎች ላይ ዘመን የማይሽረው ግፍና ጭካኔ በመፈጸም 800ሺ የሚጠጉትን ከምድር ላይ ለዘለአለሙ አሰናብቷቸዋል። ይህ ደግሞ የዘር ማጥፋት ወንጀል በመሆኑ አጥፊዎቹ በተለያዩ የፍትህ አደባባዮች ተከሰው ቅጣታቸውን ለመቀበል በቅተዋል። ነገር ግን ይህ ብቻውን በህዝቡ ውስጥ ስር የሰደደውን ቁስል እንዳማይሽረው በመታመኑ ሩዋንዳ የሽግግር ፍትህን በመከተል አመርቂ ስራ ሰርታለች። በተለይም ክስና ይቅርታ ትልቅ ቦታ ነበራቸው። በክስ ሂደቱ ሁሉንም ተጠያቂ ማድረግ ቢከብድም በዋናነት ተሳታፊ የነበሩትን በመለየትና ተጠያቂ በማድረግ ፍትህ እንዲሰፍን ተደርጓል። መንግስት ውጫዊና ውስጣዊ ግፊት ቢበዛበትም ከፍተኛ ግፍ የፈጸሙትን በመለየት እንዲቀጡ አድርጓል። ይቅርታውንም በተጠና መንገድ በማከናወን ለጥቂቶች ምህረት አድርጓል። በጊዜ ሂደት የእስራት ጊዜአቸውን ላገባደዱ፣ ለአዛውንቶች፣ ለታማሚዎችና ለወጣቶች ምህረት በማድረግ ቁርሾው እንዲሽር ተደርጓል። ምህረት የተደረገላቸው ሰዎች ስለብሄራዊ እርቅ፣ አብሮነት፣ ሀገራዊ ማንነትና ሰብዓዊ ክብር እንዲማሩ በማድረግ እርቁን ሙሉ ማድረግ ተችሏል። የሩዋንዳ የሽግግር ፍትህ በዋናነት እውነትን ማፈላለግ፣ ነገሮችን መልሶ ማስታወስ ወይም የመታሰቢያ ቦታዎችን በመመስረትና ቀን በመሰየም ሁኔታው ታስቦ እንዲውል ማድረግ፣ መልሶ ማቋቋምና እርቅ ማውረድ የተቋማት ማሻሻያ ማድረግ ላይ ያተኮረ ነበር። ሴራሊዮን እኤአ ከ1991 አስከ 2002 የዘለቀው የሴራሊዮን የእርስ በርስ ግጭት በትንሹ የ100ሺ ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ አልፏል። ሌሎች በ100ሺ የሚቆጠሩ ዜጎችን ለከፋ የአካል ጉዳት፣ ድህነትና የአዕምሮ መቃወስ ዳርጓል። ግጭቱ የተጀመረው ራሱን “የተባበሩት አብዮታዊ ቡድን” ብሎ በሚጠራው የታጣቂዎች ስብስብ ሲሆን በወቅቱ ቡድኑ በላይቤሪያ መንግስት ይደገፍ እንደነበር ይነገራል። የተቃውሞአቸው መነሻ ደግሞ የመንግስት ብልሹ አስተዳደር፣ የገጠሩ ማህበረሰብ ከኢኮኖሚና ፖለቲካ ተሳትፎ መገለል እና መጠነ ሰፊ የህግ ጥሰቶች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ። የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሃብት በተለይም የአልማዝ ማዕድኗን በህገወጥ መልኩ ሲበዘብዙ የነበሩ አመራሮች ቁርሾውን በማባባስ ህልውናቸውን ለማስቀጠል ቢጥሩም እኤአ በ2002 በተደረሰ የሰላም ስምምነት ከ 76 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን በማስረከብ ህብረተሰቡን እንዲቀላቀሉ ተደርገዋል። በዚያው ዓመት የሴራሊዮን የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን የተቋቋመ ሲሆን በተመሳሳይ የሴራሊዮን ልዩ ችሎት ተመስርቷል። ሴራሊዮን በእርስ በርስ ግጭት ውስጥ በነበረችባቸው 12 ዓመታት አራት መፈንቅለ መንግስት የተካሄደባት ሲሆን የስልጣን መንበሩን የተፈራረቁበት የተለያዩ ወታደራዊ አመራሮች ለችግሩ መፍትሄ ከማበጀት ይልቅ በቤንዚን ላይ እሳት የሚያርከፈክፉ ሆነው ታይተዋል። በሴራሊዮን ለደረሰው እልቂት እኩል ኃላፊነት የሚወስዱት መንግስትና ታጣቂዎች በወቅቱ ሴቶችን በመድፈር፣ ህፃናትን በግዳጅ ለጦርነት በመመልመል፣ ንብረት በማውደምና በ100ሺ ለሚቆጠሩ ሰዎች መሞት ተጠያቂ ተደርገዋል። ከዚህ ባለፈ በቅድሚያ ታጣቂዎችን የጦር መሳሪያ ለማስፈታት የተሄደበት ርቀት ለሰላም መስፈን ትልቅ እገዛ ማድረጉ የሚገለጽ ሲሆን ከ70 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎችን መሳሪያ ማስፈታት መቻሉ ግጭቱን ለማስቆም በራሱ ታላቅ ስኬት ነበረው። በወቅቱ ግፉን የፈጸሙት ታጣቂዎች በመንግስት ቅጣታቸውን እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን ህብረተሰቡም ወንጀለኞችን ከማህበረሰቡ በማግለል የስነ ልቦና ቅጣት እንደጣለባቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በዚህም ታጣቂዎቹን ወደ ህብረተሰቡ መልሶ ለመቀላቀል የተደረገው ጥረት በፈተና ቢታጀብም በህዝቡ ይሁንታ ውጤታማ ሆኗል። በሴራሊዮን የሽግግር ፍትህን ለማስፈን የተቋቋሙት የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን፣ የሴራሊዮን ልዩ ፍርድ ቤት፣ በፀጥታ ተቋማት ላይ የተደረገው ማሻሻያ፣ የመልሶ ማቋቋምና የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ምስረታ ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው። የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን በተሰጠው ስልጣን መሰረት ተጎጂዎችን ከሰቆቃ መታደግና ችግሩን በዕርቅ መፍታት፣ ብዙሀኑ ላይ ለደረሰው ግፍ ምላሽ መስጠት፣ ግፉ በቀጣይ እንዳይደገም መፍትሄ ማበጀት ላይ አተኩሮ ሰርቷል፡፡ በዚህም ከተጎጂዎች ቃለ ምልልስ በመነሳት በደረሰበት ድምዳሜ የመንግስት አካላት የመልካም አስተዳደር መጓደል፣ ሙስና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ከነፃነት በኋላ የነበረው አመራር ብቃት ማነስ ለብጥብጡ መንስኤ እንደሆነ አመላክቷል። ልዩ ፍርድ ቤቱም በቅድሚያ ተጎጂዎችን ሰብስቦ በማናገር እንዲሁም የሲቪል ማህበራትን ህብረተሰቡንና መገናኛ ብዙሃንን በማካተት ሁሉንም የሚያስማማ ውሳኔ በመስጠት ችግሩ ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ መፍትሄ እንዲያገኝ አስችሏል። የመልሶ ማቋቋም ሂደቱ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበርና ልዩ በጀት በመመደብ የተከናወነ ሲሆን የተጎጂዎችን ሰቆቃ ሊጠግን በሚችል መልኩ መተግበሩንም ብዙዎች ይመሰክራሉ። በዚህም ተጎጂዎች ነፃ የጤና አገልገሎት፣ ትምህርት፣ መኖሪያ ቤትና መቋቋሚያ እንዲያገኙ ተደርጓል። በአብነት የተነሱት የሩዋንዳና ሴራሊዮን ተሞክሮዎች የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭቶችን ያስተናገዱ ሀገራት የተሻለ ነገን እንዲገነቡ ሁነኛ መፍትሔ ስለመሆኑ አመላካች ናቸው። በተመሳሳይ የሽግግር ሂደት ያለፉና ተሞክሮ ያላቸው የደቡብ አፍሪካ እና ጋምቢያ ምሁራንም ይህንኑ እውነት የሚያረጋግጥ ሀሳባቸውን ለኢዜአ ሰጥተዋል። በደቡብ አፍሪካው ፍሪታውን ዩኒቨርሲቲ የፍትሕና ዕርቅ ኢንስቲትዩት ኃላፊ እና በአፍሪካ ጥናትና ምርምር የካበተ ልምድ ያላቸው ፕሮፌሰር ቲም ሙሪቲ በአፍሪካ ሽግግር ፍትህ ዙሪያ ጥልቅ ምርምር አድርገዋል። ኢትዮጵያ ታሪካዊና የአፍሪካ ተምሳሌት ሀገር ናት የሚሉት ፕሮፌሰሩ፤ የገጠማትን ችግር ለመፍታት የሽግግር ፍትህ ሂደት መጀመሯን አድንቀዋል። የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭትና ግፎችን ባሳለፉ ማህበረሰቦች ትናንትን በይቅርታ የነገውን ተሰፋ ለመሻገር አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን በማንሳት ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ፣ ባርነት እና ቅኝ ግዛት የጭቆና ስርዓት ነጻ ስትወጣ ስርዓቱ በጥቁሮች ላይ ለፈጸመው ግፍ፣ መገለልና ብዝበዛ መፍትሄ ለመስጠት ሽግግር ፍትህ ሂደት መተግበሩን ይጠቅሳሉ። ፕሮፌሰር ሙሪቲ፤ የወቅቱ ፕሬዝዳንት ኔልሰን ማንዴላ በጥቁሮች ላይ የተፈጸሙ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት መልክ ለመስጠት ብሎም ህዝባዊ አብሮነት እንዲቀጥል በሊቀጳጳስ ዴዝሞንድ ቱቱ መሪነት የዕውነትና ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን መቋቋሙን ያስታውሳሉ። የሽግግር ፍትሕ ሂደቱ ከአፈጻጸም ጋር የተያያዙ ክፍተቶች ቢኖሩበትም አካታችና የአገሪቱን የቀጣይ ጉዞ ለመቀየስ መሰረት የጣለ እንደነበር ገልጸዋል። ይህም ኢትዮጵያ ተሞክሮ ልታደርገው የምትችለው ነው ይላሉ። በጋምቢያ በቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ያህያ ጃሜህ ዘመነ መንግስት ለ22 ዓመታት የተፈጸሙ ግፎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት የፈቱት የዕውነት፣ ዕርቅና ካሳ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ጋምቢያዊው ዶክተር ባባ ጋሌህ ጃሎው፤ የሽግግር ፍትህ አስፈላጊነት በተለይም ኢትዮጵያን ለመሰሉ ሀገራት አጠያያቂ አለመሆኑን ይላሉ። በተመሳሳይ በጋምቢያ አምባገነን መንግስት የተፈጸሙ በደሎችን መልክ ለማስያዝ የተቋቋመው የዕውነት፣ ዕርቀ ሰላምና ካሳ ኮሚሽን ዜጎች ዕውነቱን እንዲረዱ፣ በዳዮች እንዲጠየቁና ተበዳዮች እንዲካሱ የሚያስችል ሰነድ ለሀገሪቷ መንግስት ማቅረቡን ዶክተር ባባ ጋሌህ ይገልጻሉ። እነዚህ ምሁራን ኢትዮጵያ ለማድረግ ያሰበችው የሽግግር ፍትህ ሂደት ከአፍሪካ ሕብረት የሽግግር ፍትሕ ፖለሲ እና የሀገራትን ልምድ የቀመረ፣ አካታች፣ ተበዳዮችን የሚክስና ሀገርና ህዝብ ወደፊት በሚያሻግር አግባብ እንዲፈጸም አስተያየታቸውን ጠቁመዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራኑ ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ለሚመለከተው አካል እንደሚያጋሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያን ባለፉት ጥቂት ዓመታት በህዝቦች የተባበረ ክንድ ለውጥ በማምጣት አዲስ ምእራፍ የጀመርንበት፣ አዲስ መንግስት ስልጣን ተቀብሎ ያለፉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በይፋ በማመን ይህንኑ ለማሻሻል ቃል የገባበት፣ የዲሞክራሲ ሽግግር ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት የተጀመሩበት እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት የደረሱ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ለማለፍ መንገድ የጀመርንበት ወቅት ላይ መሆናችን ይታወቃል። የሽግግር ፍትህ የተበዳዮችን እምባ ከማበስ ባለፈ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ በማስቀመጥ ከቂም በቀል የጸዳ ትውልድ ለመፍጠርና ለአገረ መንግስት ግንባታ በጋራ ለመሰለፍ መፍትሄ መሆኑን ከላይ የተጠቀሱት አብነቶች ምስክሮች ናቸው። ለአፍሪካ ጉዳዮች አፍሪካዊ መፍትሄን የምታስቀድመው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገራት ተሞክሮዎችን በመቀመር፣ ካለፈችባቸው መንገዶች ትምህርት በመውሰድ፣ ውጤታማ የሆነ የሽግግር ፍትህ ስርዓትን እውን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል። የሽግግር ፍትሕ በተለይም በሽግግር ላይ ያሉ ሀገራት ህዝቦች ከነበሩበት ግጭት እንዲሁም ከደረሰባቸው ግፍ እና ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ወጥተው ወደ አዲስ ሰላማዊ እና አብሮነት ጉዞ ለመጀመር የሚደረግ የፍትሕ ክዋኔ አይነት በመሆኑ በትኩረት ሊሰራበት ይገባል።          
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 2178
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
ትንታኔዎች
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች
May 26, 2023 104
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች ሰለሞን ተሰራ አውሮፓዊያን ለጥቁሮች ከነበራቸው ዝቅተኛ አመለካከት በመነጨ እብሪት “የአፍሪካ ቅርምት” እየተባለ በሚታወቀው አጀንዳቸው አህጉሪቱን ለመከፋፈል ቁጭ ብለው የመከሩት በ18ኛው ክፍለ ዘመን ማገባደጃ ላይ ነበር፡፡ በጀርመን መዲና በርሊን የተሰበሰቡት ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ፖርቱጋል፣ ቤልጂየም እንዲሁም ዘግይተው የተቀላቀሉት ጣልያን እና ጀርመን አቅማቸው የፈቀደውን ያህል አህጉሪቱን በመቆጣጠር ሀብቷን ለመመዝበር ሕልም አንግበው የወል ቃል ገብተዋል፡፡ እነዚህ ሀገራት አፍሪካን አንድ አድርጎ ለመግዛት ሕልማቸውን አስተሳስረው ቢነሱም በመሀከላቸው በነበረው ፉክክር የተነሳ ምኞታቸው ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡ አውሮፓውያን በአህጉሪቱ የዘረጉትን የቅኝ አገዛዝ መዋቅር በጣጥሶ ለመጣል በቅድሚያ አህጉሪቱን አንድ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን የሚያምኑ አፍሪካውያን መሪዎች ህብረት ለመመስረት ቢነሱም ሀሳባቸው ለሁለት በመከፈሉ ሁለት ቡድን እንዲፈጠር ምክንያት ሆኖ አልፏል፡፡ ይህን ተከትሎ የተፈጠሩት ሁለት ቡድኖች በአንድ ወገን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ሀገራቱ በፍጥነት ተዋሕደው አፍሪካ አንድ ልትሆን ይገባል የሚለው የካዛብላንካ ቡድን፤ እንዲሁም አንድ ከመሆን በፊት ሌሎች ትብብሮች ሊቀድሙ ይገባል የሚለው የሞኖሮቪያ ቡድኖች ነበሩ፡፡ ሁለቱም ቡድኖች የአፍሪካ አንድነት እንዲመሰረት ጽኑ አቋም ቢኖራቸውም፣ እንዴት ነው መመስረት ያለበት የሚለው ጥያቄ ግን የልዩነታቸው ወሰን ሆኖ ወደ ንትርክ የገቡበት ጊዜ ነበር። በ1961 የተመሰረተው የካዛብላንካው ቡድን በጋናዊው ኩዋሜ ኑኩርማህ የሚመራ ሲሆን ዓላማቸው አፍሪካ አሁን መዋሃድ (አንድ መሆን) አለባት የሚል ሲሆን ከአባላቱ መካከል ጊኒ፣ ሊቢያ፣ ግብጽ፣ ሞሮኮ፣ ማሊ፣ አልጄሪያ ይገኙበታል። የሞኖሮቪያው ቡድን ደግሞ በሴኔጋላዊው መሪ ሴንጎር የሚመራ ሲሆን በስሩም ሃያ አራት ሃገራትን፣ ማለትም ናይጄሪያ፣ ሴኔጋል፣ ካሜሮን፣ አይቮሪኮስት፣ ቶጎ፣ ላይቤሪያ እና ሌሎች ብዙ የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበሩ ሃገራትን ያቀፈ ነበር፡፡ የዚህ ቡድን የውህደት መርህ ደግሞ “አፍሪካ መዋሃድ የምትችለው በኢኮኖሚያዊ ትብብር ሆኖ በቀስታ በምታደርገው ጉዞ ነው” የሚል ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ወገኖች ፍጥጫ አርግባ ወደ ውህደት ያመጣቻቸው ኢትዮጵያ ስትሆን ድርጅቱ የዛሬ 60 ዓመት እ.ኤ.አ ግንቦት 25 ቀን 1963 ሲመሰረት የመጀመሪያው ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት አጼ ኃይለስላሴ ነበሩ፡፡ የፓን አፍሪካኒዝም ልጅ የሆነው የያኔው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋና ዋና ዓላማዎቹ ቅኝ ገዢዎችን ማስወገድ፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል አንድነትና ሕብረትን ማበረታታት፣ ለአፍሪካዊያን የተሻለ ህይዎት እና እድገት ለማምጣት፣ ሉዓላዊነትንና የወሰን አንድነትን ማስጠበቅ፣ ሰብዓዊ መብቶችን ማስከበር፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል የሚካሄዱትን ግጭቶች በሰላማዊና በዲፕሎማሲ መፍታት የሚሉ ነበሩ። የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀደምት መሪዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን የሚተካ አዲስ አህጉራዊ ድርጅት ለመመስረት እ.አ.አ በ1999 ያሳለፉትን ውሳኔ መሠረት በማድረግ የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ በሐምሌ 2002 በደርባን ደቡብ አፍሪካ በይፋ መመስረቱ ይታወቃል። የአፍሪካ ኅብረት ራዕይም፤ የተቀናጀች፣ የበለጸገች እና ሰላማዊ፣ በራሷ ዜጎች የምትመራ እና በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ተፎካካሪ የሆነች አፍሪካን መመስረት ነው። እ.አ.አ በ2013 የአፍሪካ መሪዎች በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት አጀንዳ 2063 የተሰኘውን አህጉራዊ እቅድ ነድፈዋል። እቅዱ ከሁሉም በላይ በአህጉሪቱ ላይ የሚቃጡ ጦርነቶችን ማስቆምና መሰረተ ልማት ዝርጋታ ላይ የሚያተኩር ሲሆን በአህጉሪቱ ዜጎች ከአገር አገር ነፃ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ራዕይ የሰነቀ ነው። ሌላው ወሳኝ ፕሮጀክት የአፍሪካ ነፃ ገበያ ምህዳርን መክፈት ሲሆን ይህ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ በርካታ አገራትን አሳታፊ በማድረግ የዓለም ትልቁ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ ስምምነት ሲሆን አሁን ላይ ተግባራዊ ሊደረግ ከጫፍ ደርሷል። ይህ የነፃ ገበያ ስምምነት በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ለማስፋፋት የታለመ ከመሆኑ በላይ የሀገራቱን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድገው ታምኖበታል። የአፍሪካ ነፃ ገበያ ስምምነት አገራት የውስጥ ገበያቸውን ለመጠበቅ ባወጧቸው ቀደምት ህጎችና እንዲሁም በደካማ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ምክንያት ከፍተኛ ችግር እንደሚገጥመው አስተያየት ቢሰጥበትም ያዘለው ተስፋ ግን ከችግሩ የገዘፈ ነው። ሁሉንም የአፍሪካ አገራት መዲናዎች እና የንግድ ማዕከሎች በፈጣን የባቡር መስመር ማገናኘት፣ በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ማበረታታት እንዲሁም የአፍሪካ አገራት በዓለም አቀፍ የንግድ ገበያ ያላቸውን ተሳትፎ ማጎልበት አጀንዳ 2063 ካስቀመጣቸው ግቦች መካከል ቀዳሚዎቹ ናቸው። አፍሪካውያን በአህጉሪቱ በነፃነት የመዘዋወር፣ የመስራት እና የመኖር መብት እንዲኖራቸው ማድረግ እንዲሁም በአህጉሪቱ ያሉ ግጭቶችን ማስቆም እና ሌሎችም በርካታ ግቦች በእቅዱ ላይ ተቀምጠዋል። ነገር ግን የአፍሪካ ሕብረት እነዚህን አጀንዳዎች ለማስፈፀም በእጅጉ እየተፈተነ ሲሆን ለዚህ ዋነኛ መንስኤው የሕብረቱ አባል አገራት በገቡት ስምምነት መሰረት ነገሮችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ማስገደድ አለመቻሉ እንደሆነ ይነገራል። ተንታኞች እንደሚሉት የአፍሪካ አገራት ያለባቸውን ከፍተኛ የእዳ ጫና ለመክፈል የሚያደርጉት ትግል ትልቁን አህጉራዊ አጀንዳ ችላ እንዲሉ ግድ ብሏቸዋል። የህብረቱ በጎ ርምጃዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋነኛ ዓላማው በቅኝ አገዛዝ ስር የነበሩ ሀገሮችን ነጻ ማውጣት ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር የተሳካ ተግባር ማከናወኑ በታሪክ ሲወደስለት የሚኖር ስኬቱ ነው፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆኖ ከሞላ ጎደል ውጤት ያስመዘገበባቸው ዘርፎች አሉ። ሀ. ሰላምና ደህንነት የአፍሪካ ህብረት ሰላምንና ደህንነትን ለማረጋገጥ በተለይም የአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ኃይል በተለያዩ የአህጉሪቱ ክፍሎች ያደረገው ተጋድሎ በአዎንታ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ ለማሳያም ላይቤሪያ፣ ሴራሊዮን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን ተሰማርቶ የነበረው የአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ኃይል ከሌሎች የተሻለ አፈጻጸም እንዳለው ይገለጻል፡፡ ለ. ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በተለያዩ የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መረጋጋት እንዲፈጠር ለማድረግና ዴሞክራሲን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት እና የተፈጥሮ ሃብቷ ለፈጣን ዕድገቱ በምክንያትነት ይነሳሉ፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋና ኢኮኖሚው እንዲያድግ የወሰዳቸው ተቋማዊ እርምጃዎች ወሳኝ ሚና ሲኖራቸው የአፍሪካ ልማት ባንክን በማቋቋም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መደገፉ ተጠቃሽ ነው፡፡ በተለይም ለመንገድና ለውኃ ሃይል ማመንጫ ባንኩ ያደረገው ድጋፍ ተገቢው ቦታ የሚሰጠው ሲሆን ለአፍሪካ የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነት መሻሻል ማነቆ የሆኑትን ታሪፍ በመቀነስም የተሻለ ስራ ሰርቷል፡፡ ሐ. ዓለም አቀፍ ተሰሚነት የአፍሪካ ህብረት በዓለም አቀፍ መድረኮች በተለይም የዓለም ኢኮኖሚንና የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከተ አንድ አቋም መያዙ ከህብረቱ ታሪክ ተጠቃሽ ስኬቶች አንዱ ነው፡፡ አፍሪካ የአየር ንብረት ተፅዕኖውን ለመላመድና ለመቋቋም የሚረዳትን ተገቢውን ክፍያ እንድታገኝ ህብረቱ ውጤታማ ስራ ሰርቷል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ የልማት ችግሮችን ለመፍታት ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ጥረት አድርጎ ባስመዘገበው ውጤትም ይመሰገናል፡፡ በተለይም የተባበሩት መንግስታት የሚሊኒየም የልማት ግቦች እንደ መገለጫ ይነሳሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ለማግኘት እንዲሁም የአፍሪካ ድምጽ የሚጎላበት ሚዲያ እንዲኖር የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች በአዎንታ የሚነሱ ናቸው። መ. ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ ዴሞክራሲንና መልካም አስተዳደርን በማስፈን በኩልም ከነጉድለቶቹም ቢሆን በመልካምነት የሚጠቀሱ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይገለጻል፡፡ በአህጉሪቷ ከ30 ዓመት በፊት አምስት ሀገራት ብቻ ዴሞክራት የነበሩ ሲሆን አሁን ከአፍሪካ ሀገሮች 95 በመቶዎቹ ወቅቱን ጠብቀው ምርጫ የሚያካሂዱ ሀገራት ናቸው፡፡ የምርጫ ታዛቢዎችን በአባል ሀገራት እየላከ መታዘቡም እንደ ጥሩ ጅምር መታየት ያለበት ነው፡፡ በተለይ ደግሞ የአፍሪካ የእርስ በርስ መገማገሚያ መድረክን /APRM/ ማቋቋሙ በጥንካሬ ሲነሳ በዚህ መድረክ አማካኝነት ሀገራት በራሳቸው ተነሳሽነት ስለሀገራቸው የመልካም አስተዳደር አፈጻጻም ሪፖርት የሚያደርጉበትና ልምድ የሚለዋወጡበት እድል ተፈጥሯል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በሀገሮች ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ያለመግባት መርህ በማሻሻል በመፈንቅለ መንግስት የሚመጡ ቡድኖችን ላለመቀበል መወሰኑ ህብረቱ በዴሞክራሲ ላይ ያለውን አቋም ያሳያል፡፡ መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች በርግጥ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት አንግቦት ከነበረው አባል ሀገራቱን ከቅኝ ገዥዎች ነፃ የማውጣት ተልዕኮ አንስቶ እስከ ወቅታዊው የአየር ንብረት ለውጥ ድርድር አበጀህ የሚያስብሉትን ስኬቶች አስመዝግቧል፡፡ በቀዝቃዛው የዓለም ጦርነት ጊዜ አብዛኛው ሃገራት የገለልተኛ ሀገሮች ማህበር አባል ቢሆኑም የአፍሪካ ሀገሮች እርስ በእርሳቸው ተከፋፍለው አፍሪካን የጦርነት አውድማ አድርገዋት ነበር፡፡ አንዱ የአፍሪካ ሀገር የምዕራቡ ካምፕ ደጋፊ ከሆነ ሌላኛው የምስራቅ ካምፕ ደጋፊ ነበር፡፡ ሁለቱም ካምፖች ለርዕዮተ ዓለም ተከታዮቻቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ በማድረግ አፍሪካ እርስ በእርስ እንድትባላ አድርገዋል፡፡ ይህም ህብረቱ የተቀደሰ ሃሳብ ቢኖረውም የማስፈፀም አቅሙ ያን ያህል የተጠናከረ አለመሆኑን ያሳያል፡፡ ለህብረቱ የማስፈጸም አቅም ማነስ አንደኛው ምክንያት ከአባል ሀገራት የሚጠበቀውን ገንዘብ በአግባቡ አለመሰብሰቡ ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የህብረቱ የ2023 በጀት 654 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር እንዲሆን በዛምቢያ በተደረገ ጉባኤ ውሳኔ የተላለፈ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 60 በመቶ የሚልቀው በጀት ከለጋሾች እንደሚሰበሰብ በወቅቱ ይፋ ተደርጓል፡፡ በሌላ በኩል አፍሪካ በየዓመቱ 50 ቢሊዮን ዶላር በሙስና እንደምታጣ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ 1 በመቶ እንኳን ማዳን ቢቻል የህብረቱን የ2 ዓመት ወጪ መሸፈን ይቻላል ይላሉ ባለሙያዎች፡፡ ጥቂት በማይባሉ የህብረቱ አባል ሀገራት ሙስና ዛሬም አደጋ መሆኑ፣ የርስ በርስ ግጭት በሚፈለገው ደረጃ አለመፈታቱ፣ ድህነት አሁንም የአህጉሪቱ ቀንደኛ ጠላት መሆኑ፣ የትምህርትና ጤና አገልግሎቶች ተደራሽ አለመሆንና ጥራቱም የተጓደለ መሆን፣ በህብረቱ የሚወሰኑ ውሳኔዎች አፈጻጸም የተለያየና የሚፈለገውን ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ ውስንነት ያለበት መሆኑ ወዘተ የህብረቱና አባል ሀገራት ጉድለት ሆነው ቀጥለዋል። ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች የአፍሪካ ህብረት ከስኬቱም ሆነ ከልምዱ ለመማር የሚያስችለው ከግማሽ ክፍለ ዘመን የዘለቀ የእድሜ ባለፀጋ ሆኗል፡፡ እናም የወደፊት አቅጣጫውን ሲተልም ያለፈውን ጉዞ ዞር ብሎ ማየት፤ የቆመበትን ነባራዊ ሁኔታ ጠንቅቆ መረዳትና መጭውን አቅርቦ ማሰብ ይጠበቅበታል። ለዚህ ደግሞ የማስፈጸም አቅምን ማጠናከር፣ ለስራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት መስጠት፣ ተሳትፎን ማሳደግ፣ የገቢ አቅምን ማሳደግ ወሳኝ ናቸው። ሀ. የማስፈጸም አቅም የአፍረካ ህብረት ከአፍሪካ አንድነት ደርጅት የተሻለ አደረጃጀትና አሰራር እንዳለው የሚቀበሉ አሉ፡፡ ለምሳሌ በሀገሮች ጣልቃ ያለመግባት መርህን በማሻሻል ህብረቱ በመፈንቅለ መንግስት የመጡ ቡድኖችን በአባልነት አይቀበልም ነገር ግን በአፍሪካ አሁንም የእርስ በርስ ግጭት የሚታይባቸው ሀገሮች አሉ፡፡ ስለሆነም ይህንኑ ችግር ሊቀርፍ የሚችልና ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበ አደረጃጀትና አሰራር ሊኖረው ይገባል፡፡ የህብረቱ በጀት በሌሎች አካል መሸፈን አሉታዊ ተፅዕኖ ስለሚኖረው አባል ሃገራት የሚጠበቅባቸውን መዋጮ በወቅቱ በመክፈል የህብረቱን የማስፈፀም አቅም ማሳደግም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለ. የስራ እድል ፈጠራ የአፍሪካ ህብረት በተለይ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ማዕከል ያደረገ እድገትን ማበረታታት ግድ የሚለው ወቅት አሁን ነው፡፡ ሆኖም ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ከማረጋገጥ አኳያ ብዙ የሚቀሩ ስራዎች እንዳሉ እሙን ነው። በተለይም ወጣቶችን ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ መሰራት ያለባቸው የቤት ስራዎች በአግባቡ አለመሰራታቸው በጉልህ ይጠቀሳሉ፡፡ እንደ አፍሪካ ኢኮኖሚ አውትሉክ መረጃ በአፍሪካ እድሜያቸው ከ15 እስከ 25 ዓመት ያሉ ወጣቶች ከአህጉሪቱ አጠቃላይ ህዝብ ከ70 ከመቶ በላይ ይሸፍናሉ፡፡ የዓለም ባንክ ያወጣው መረጃ እንደሚያሳየው በአፍሪካ 200 ሚሊዮን የሚጠጉ እድሜአቸው ከ15 እስከ 25 የሚጠጋ ወጣቶች ሲኖሩ ከነዚህ መካከል 60 በመቶ የሚጠጉት ስራ ፈላጊ መሆናቸው ደግሞ ህብረቱ የሚጠብቀውን ከባድ ስራ ያሳያል፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በየሃገሮቹ ለወጣቶች ምን ያህል የስራ እድል እንደተፈጠረ መጠየቅን የእርስ በእርስ መገማገሚያ መድረኩ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ ሊያደርገው እንደሚገባ ምሁራን ይመክራሉ፡፡ ሐ. የህዝብ ተሳትፎና የውክልና ዴሞክራሲ ህብረቱ ሊያሳካ ያሰባቸውን ግቦች እውን ማድረግ የሚቻለው በሁሉም የነቃ ተሳትፎ መሆኑ አያጠያይቅም። በመሆኑም አባል አገራት ችግሮችን ከመለየት ጀምሮ እስከ ክትትልና ግምገማ ስርአት ህብረተሰቡን በሁለንተናዊ መርሃ ግብሮች ማሳተፍ ይገባቸዋል፡፡ ይህ ሲደረግ ነው በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ ያሉ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የፈጠራ ችሎታዎችን ማውጣትና ሀገሬ ለእኔ ምን አድርጋለች ሳይሆን እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ የሚሉ ዜጎችን መፍጠር የሚቻለው፡፡ በአፍሪካ በየቦታው የሚታዩ የእርስ በእርስ ግጭቶች መንስኤ በዋነኛነት የህዝብ ፍላጎት አለመሟላት ሲሆን በተለይም የአናሳዎች መብት አለመከበር የግጭት መንስኤ ሲሆን ይታያል፡፡ ለዚህ ደግሞ በየአካባቢው አስተዳደር ህዝቡን በየጊዜው ማማከር ያስፈልጋል፡፡ መ. ውስጣዊ የገቢ አቅምን ማሳደግ በዋናነት አራት የገቢ ምንጮች ያሉ ሲሆን እነሱም የሃገር ውስጥ ብድር፤ ግብርና ታክስ፣ የውጭ ብድር እና እርዳታ ናቸው፡፡ ከግብርና ታክስ በስተቀር ሌሎች የገቢ ምንጮች አሉታዊ ተጽዕኗቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ግብርና ታክስን በአግባቡ መሰብሰብ የአንድ ሀገር የሁለንተናዊ ብቃት መለኪያ ነው፡፡ ግብርና ታክስ የመንግስት ወጪ በመሸፈን ነጻነትን ከማጎናጸፉም በተጨማሪ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍልን ለማረጋገጥ ሁነኛ መሳሪያ ነው፡፡ አልጀዚራ ባወጣው መረጃ መሰረት አፍሪካ በእርዳታና በብድር ከምታገኘው ይልቅ በታክስ ማጭበርበርና ስወራ የምታጣው ከ10 እጥፍ በላይ ይበልጣል፡፡ ለዚህ ደግሞ የታክስ ህጎች ክፍተት መኖርና በሙስና የተጨማለቁ ባለስልጣናት እንዲሁም ብቃት ያለው የሰው ኃይል አለመኖር አስተዋፆኦ ያደርጋሉ፡፡ የገቢ አሰባሰብ ስርአቱን በማሻሻል የአፍሪካን ነጻነት ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአፍሪካን የእርስ በርስ ንግድ ማስፋፋት፤ የታሪፍና ቀረጥ ምጣኔን ማሻሻል፤ የወጪ ገበያ የምርት አይነቶችን ማስፋትና ሃገራቱን በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር የየሃገራቱን የተናጠል ጥረትና የህብረቱን አመራሮች የጋራ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራቱን በማስተባበር ባለፉት 60 ዓመታት ያለፈበትን የውጣ ውረድ ጉዞ በማጤን የተሻለ ነገን ለመገንባትና የአፍሪካን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከትላንቱ በበለጠ መትጋት ይገባዋል።      
"እንሰትና ሁለገብ ጠቀሜታው"
May 6, 2023 851
በፍሬዘር ጌታቸው እንሰት በኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ያስቆጠረ፤ በተለይ በደቡቡ የሀገሪቱ ክፍሎች በስፋት የሚመረት ተክል እንደሆነ የታሪክ ድርሳናትና በዘርፉ የተካሄዱ ጥናቶች ያስረዳሉ። እንሰት በደቡብ የሀገራችን ክፍል በሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝብች ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ነውና የምግብ ዋስትና አለኝታ ተደርጎ የሚወሰድ ተክል ነው። ተፍቆ ለምግብነት ወሳኝ የጤንነት መጠበቂያና የጥንካሬ መሰረት ተደርጎ ይወሰዳል። የእንሰት ተክል የሚጣል ነገር የለውም። ተረፈ ምርቱ ለእንሰሳት መኖ ጭምር ያለው ፋይዳ የላቀ ነው። እያንዳንዱ የእንሰት ተክል ክፍል ከምግብነት ባሻገር ለተለያዩ አገልግሎቶች ይውላል። የእንሰት ተክል ለም አፈር በንፋስና በጎርፍ ታጥቦ እንዳይወሰድ የመከላከል አቅሙ ከፍተኛ ነው። ከዚህም ባሻገር የአፈር ለምነትን እና እርጥበት ጠብቆ በማቆየት ለምርታማነት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው በመሆኑ ከደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች ሕዝቦች ጋር ያለውን ቁርኝት ዘመን ተሻጋሪ ያደርገዋል። ለአብነትም እንሰት በወላይታ ብሄር ከሰውና ከእንስሳት ምግብነት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን በአካባቢው "ኡታ" ተብሎ ይጠራል። እንሰት ወይም "ኡታ" የባለፀጋነት መገለጫም ነው። የመኖሪያ ቤቱን ዙሪያ፣ ቀዬውን በእንሰት የከለለና ያስዋበ፣ ማሳውን በእንሰት ያለማ አባወራ ባለጠጋ እንደሆነ ይታመናል። አባወራውም "አላ ኡታ ጎዳው" በማለት ይሞካሻል። እንሰት ለምግብነት፣ ለመደኃኒትነት፣ ለአካባቢ ውበት፣ ለአፈር እርጥበትና ለምነት ለመጠበቅ፣ ለእንሰሳት መኖነት፣ ለባህላዊ ቤት ስራ ጣራና ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት ያገለግላል። እንዲሁም ኮባው (ቅጠሉ) እንደ ዳቦ ለመሳሰሉት ምግብ ማብሰያና ለተለያዩ የግብርና ዉጤቶች መጠቅለያነት ግልጋሎት ይውላል። ከእንሰት ተረፈ ምርቶች የመቀመጫና የወለል ምንጣፎችን ጨምሮ በርካታ መገልገያዎች ይሰራሉ። የእንሰት ተክል በተለያዩ አካባቢያዊ ሁኔታ መብቀል ከመቻሉ ባሻገር ድርቅን የመቋቋም አቅሙ ከፍተኛ ነው። በዚህም አካባቢው ላይ ድርቅ በተከሰትበት ወቅት "ነፍስ አድን" የሚል ስያሜም ተሰጥቶት እንደነበር በታሪክ ይናገራል። የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር መለሰ መኮንን እንሰት ምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥና የልማት ችግሮችን ከማቃለል አንጻር ከፍተኛ ሚና ያለው ነው ይላሉ። ተክሉ በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብና በሲዳማ ክልሎች በስፋት እንደሚለማና በሀገሪቱ ከ3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በላይ በተለያየ የእንሰት ዝርያ መሸፈኑን ያስረዳሉ። ከሀገሪቱ ህዝቦች ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የእንሰት ተዋፅኦን የሚመገቡና የሚገለገሉ ናቸው። የእንሰት ተክል በባህሪው የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም የከፍተኛ አቅም ያለው በመሆኑ፤ ለዝናብ እጥረትና ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ተክሉን በስፋት በማልማት የምግብና ዋስትናን በዘላቂነት ማረጋገጥ ይቻላል ይላሉ። እንሰትን ለምግብነት ከመጠቀም ባሻገር ለገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ ሀብት በመሆኑ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የተሻለ አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ጥረት ማድረግ ይጠይቃል ሲሉ ያስረዳሉ ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር መለሰ። እንሰት በአካባቢው ማስገኘት ከሚገባው ጠቀሜታ አንፃር ሲታይ እየሰጠ ያለው ጥቅም ከአቅም በታች ነው የሚሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የእንሰት ሰብል ተመራማሪ ዶክተር አብርሃም ቦሻ ናቸው። በመሆኑም የእንሰትን ምርታማነት ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲው የምርምር፤ የማህበረሰብ አገልግሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን በትኩረት እየሰራ ነው ይላሉ። በኢትዮጵያ ከባህር ጠለል በላይ ከ1 ሺህ 500 እስከ 3 ሺህ 100 ሜትር ከፍታና አማካይ የዓመት ዝናብ መጠን ያለው አካባቢ ለእንሰት ተክል ምቹ ሲሆን፤ እንሰት ዝናብን የሚተካ አማራጭ የውሃ ምንጮች ባሉበት አካባቢ ከ1 ሺህ 500 ሜትር በታች በሆኑ ቆላማ አካባቢዎችም ምርት ሊያስገኝ ይችላል ይላሉ። እንደ ተመራማሪው ገለጻ እንሰት በሀገሪቱ ከሚገኙና ዋና ዋና ሰብሎች ከሚባሉት መካከል አንዱና ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው ነው። ተክሉ ተራራማ ቦታዎች ላይ ጭምር በምቾት የሚያድግ ሲሆን እንደ ዝርያው ዓይነት ከሶስት እስከ አምስት ዓመት ውስጥ ምርቱ ውጤታማ መሆን ይችላል። ዝርያው "ወንዴ" እና "ሴቴ" ተብሎ የሚከፈል ሲሆን፤ 60 ያህል የእንሰት ዝርያዎች አሉ። ከምርት አያያዝና ብቃት አንጻር ሲታይ ከእያንዳንዱ የእንሰት ተክል ከ40 ኪሎ በላይ ዱቄት ይገኝበታል። እንሰት ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ጉልህ አስተዋፅኦ ያለው ሰብል ነው፤ ከዛም አልፎ ለሰውና ለእንስሳት ከተለያየ በሽታ የመከላከልና ከጉዳት ለማገገም የሚያስችል መድኃኒት ነው። ተክሉን የማባዛት ስራ በባህላዊ መንገድ የሚከወን ሲሆን፤ የእንስሳትና ሌሎች የሚወገዱ ተረፈ ምርቶችን በመጨመር እድገቱን ውጤታማ ማድረግ ይቻላል። ከእንሰት ምርት የሚገኘው ዱቄት ቡላ ወይም በአካባቢው አጠራር "ኢቲማ" ለልጆችና ለአዋቂዎች ጤና ተስማሚ ሲሆን፣ ገንፎ፤ የክትፎ የአይብና ጎመን ማባያ ቆጮ "ኡንጫ" እንዲሁም ሙቾና ባጭራ ለምግብነት ከሚውሉት ተጠቃሽ ናቸው። የእንሰት ተክል በተለያዩ የአፈር ዓይነቶች ላይ የሚለማ፣ የአየር ንብረት ለውጡን የመቋቋም አቅም ያለው ተክል ነው። የወላይታ ዞን እንሰት አብቃይ ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ ሲሆን በተለይም በባይራ ኮይሻ፣ በቦሎሶ ሶሬና በአንዳንድ የሶዶ ዙሪያ ወረዳዎች በተደረገ የዳሰሳ ጥናት የእንሰት ተክል የመመናመንና የበሽታ አደጋ እንደተጋረጠበት ዶክተር አብርሃም አብራርተዋል። ለዚህም ምርቱን መልሶ ለማስፋፋትና ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ከዞኑ ግብርና መምሪያ ጋር በመሆን በትብብር እየተሰራ መሆኑን ያስረዳሉ። የወላይታ ዞን የግብርና መምሪያ እርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ዓለሙ እንዳሉት በወላይታ ዞን ከ28 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በእንሰት ተክል የተሸፈነ ነው። የእንሰት ተክል የሚፈለገውን ምርትና ውጤት እንዳይሰጥ ከሚያደርጉ ተግዳሮቶች መካከል ዋነኞቹ የአጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ፣ የተለያዩ ተባዮች፣ ፍልፈልና ጃርት ይጠቀሳሉ። የእንሰት አጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ በሁሉም የእንሰት አብቃይ ስነ-ምህዳር የሚገኝ፣ በሁሉም የእድገት ደረጃ ላይ ያለን የእንሰት የሚያጠቃና ከአንዱ ወደ ሌላው ተክል የሚተላለፍ መሆኑ ችግሩን የከፋ ያደርገዋል። በመሆኑም ችግሩን ለማስወገድ ጤነኛ የእንሰት ተክሎችን በላቦራቶሪ የማባዛት፣ የበሽታ አምጪ ተህዋሲያን የማጥናትና በጄኔትክ ምህንድስና በሽታን የሚቋቋም ቅንጣት ወደ እንሰት የማስገባት ሥራ እየተሰራ ነው። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣ ከሶዶ ግብርና ኮሌጅ እንዲሁም ከአረካ የምርምር ማዕከል ጋር በመሆን በጋራ እየተሰራ ነው። ኃላፊው እንዳስረዱት ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በሽታን የሚቋቋሙ ከ20 ሚሊዮን በላይ የእንሰት ችግኞችን አባዝቶ በመትከል የተሻለ ውጤት እየታየ ነው። ይህን ሥራ በማጠናከር ከእንሰት ዘርፍ ሊገኝ የሚገባውን ጥቅም ለማግኘት አርሶ አደሩ ያለውን አገር በቀል ዕውቀቱን በአግባቡ እንዲጠቀም በከፍተኛ ንቅናቄ እየተሰራ ይገኛል። በዚህም የአካባቢውን የእንሰት ሽፋን ማሳደግ ብቻ ሳይሆን የአርሶ አደሩን ጥያቄ መመለስና ጥቅሙን ለማላቅ የተጀመረው የንቅናቄ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ወሳኙ ስራ ተደርጎ እየተከናወነ ነው። ማህበረሰቡ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የአየር ንብረት ፋይናንስ-አፍሪካውያን ገፍተው ያልሄዱበት መንገድ
Feb 18, 2023 1547
/በገዛኸኝ ደገፉ/ የአፍሪካ ቀንድ ከ40 ዓመታት ወዲህ ተከስቶ አያቅም የተባለለትን የድርቅ አደጋ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ ሆነዋል። የድርቁ አደጋ የከፋበት የአፍሪካ ቀንድ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ተሸክመዋል። በተጨማሪም የከተሞች መስፋፋትና የከተሜነት የኑሮ ዘይቤን እያስተናገደች ባለችው አፍሪካ የኃይል እጥረት፣ በቂ የመሰረተ ልማት አውታሮች ዝርጋታ አለመኖር፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት፣ ሥራ አጥነት ብሎም የወንጀሎች መስፋፋት አሕጉሪቱን ክፉኛ እየፈተኗት ይገኛሉ። የገጠር መሬት ምርታማነት መቀነስ ከገጠር ወደ ከተማ ለሚደረገው ፍልሰት አንደኛው ገፊ ምክንያት ሲሆን ለመሬቱ ምርታማነት መቀነስ ሰበብ ተደርጎ በዋናነት የሚጠቀሰው ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት የሚወልዳቸው የውኃ ኃብት መቀነስና ለተከታታይ ዓመታት የሚዘልቁት የድርቅ አደጋዎች መሆናቸው ጉዳዩን ይበልጥ አወሳስቦታል። እንደ አህጉር ከ4 በመቶ ያነሰ የካርቦን ልቀት ያላት አፍሪካ 65 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ መሆን ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። ከዚህ ችግር ሙሉ ለሙሉ መውጣት ባይቻልም ትርጉም ባለው ደረጃ መቀነስ እንዲቻል አህጉሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ኃብትና ወጣት የሰው ኃይል በማስተሳሰር ለውጥ ማምጣት ግድ ይላታል። በአፍሪካ የማይቀረውን የከተሞች መስፋፋትም ሆነ የህዝቦቿን የመልማትና የመለውጥ ፍላጎት ማሟላት ካለባት የአየር ንብረት ፋይናንስን የበለፀጉ ሀገራት ገቢራዊ ሊያደርጉት ይገባል። የአየር ንብረት ፋይናንስ (Climate Finance) የአካባቢ፣ ብሔራዊ ወይም ድንበር ተሻጋሪ ፋይናንስን የሚመለከት ሲሆን ከሕዝብ፣ ከግል እና ከአማራጭ የገንዘብ ምንጮች የተውጣጣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለማስተካከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ስምምነት ነው። የኪዮቶ ፕሮቶኮል እና የፓሪስ ስምምነት ደግሞ ሰፊ የገንዘብ አቅም ካላቸው አገራት አነስተኛ የኃብት አቅም ላላቸው እና ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ አገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ስምምነት ነው። ስምምነቱ “የጋራ ግን ደግሞ ልዩነት ያለው ኃላፊነትና አቅም” በሚለው መርህ መሰረት ያደጉ አገሮች አዳጊ አገራትን ለመርዳት የገንዘብ ምንጮችን እንዲያቀርቡ ይጠይቃል። ፋይናንሱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ወሳኝ ድጋፍ እንደሚሆን ታምኖበታል። ምክንያቱም ልቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ላቅ ያለ የኢንቨስትመንት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ። በተመሳሳይ ከአሉታዊ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎች ጋር ለመላመድ እና ተለዋዋጭ ጫናዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ይጠይቃል። ከጥቂት አሥርት ዓመታት በፊት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበው የምእተ ዓመቱ የልማት ግብ ሰነድም ሆነ በቅርቡ በሚጠናቀቀው ዘላቂ የልማት ግቦች ላይ ለጉዳዩ ከፍ ያለ ትኩረት ቢሰጠውም እስካሁን ግን የፈየደው ነገር የለም። አፍሪካ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችን ለመላመድ ዓመታዊ 41 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የፋይናንስ ክፍተት ይገጥማታል። ይህን ክፍተት ለመሙላት አዲስ አበባ እያስተናገደች ባለችው 36ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ የአየር ንብረት ፋይናንስ ገቢራዊ ማድረግን ቀዳሚ ትኩረታቸው መሆን እንዳለበት የአንድ ዘመቻ (ONE Campaign) አጽንኦት ሰጥቶ ምክረ ሃሳቡን ሰንዝሯል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የአንድ ዘመቻ ዳይሬክተር ዶሪን ኒኒናሃዝዌ የአፍሪካ መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመላመድ ፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥን አስከፊ ተጽዕኖ የመቋቋም አቅም እንዲገነቡ መክረዋል። አፍሪካ ባልፈጠረችው የአየር ንብረት ለውጥ ህዝቦቿ ለከፋ ጥቃት እየተዳረጉ ይገኛሉ። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች የበለጸጉ አገሮች የገቡትን የማላመድ ፋይናንስ ድጋፍ ቃል እንዲፈጽሙ ከማግባባት ባለፈ ማሳሰብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይህ ማለት እኤአ ከ2020 እስከ 2025 በዓመት 100 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመተውን ግብ የማሳካት ተግባር የሚጠይቅ ነው። ከዚህ ባሻገር በቀጣዮቹ ዓመታት በተጨመሩ መዋጮዎች የሚስተዋሉ ጉድለቶችን መፍታት እና በግብጿ ሻርም ኤል ሼክ ከተማ ባስተናገደችው COP-27 ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ለመላመድ በእጥፍ ፋይናንስን የማቅረብ ቁርጠኝነት የማቅረቢያ ዕቅድ ሊነድፉ ይገባል ነው ያሉት። የአፍሪካ አገሮች ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ከሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ጋር ሲታገሉ ቢቆዩም አሁን ላይ “አፍሪካ በአፈፃጸሙ ላይ መጠነኛ መሻሻል አሳይታለች” ብለዋል። እናም በ36ኛው የመሪዎቹ ጉባዔ የተገኙ ስኬቶች እና የጠፉ ዕድሎች እንዲሁም የድርጅቱን ዓላማዎች ለማሳካት በአየር ንብረት ፋይናንስ በጥልቀት መክረው ለተሻለ ስኬት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዋና ዳይሬክተር አንቶኒዮ ቪቶሪኖ በአየር ንብረት ምክንያት የሚፈጠሩ መፈናቀልን ለመግታት የተሻሻሉ የመላመድ እና የተጽዕኖ ቅነሳ ተነሳሽነት ገቢራዊ ለማድረግ በአገራት መካከል ጠንካራ አጋርነትን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ያሰምሩበታል። በተለይ በአፍሪካ ቀንድ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ኑሯቸውን መሰረት ባደረጉ ህዝቦች ላይ አውደ-ተኮር መላመድ እና የመቋቋም አቅም ግንባታ መፍጠር ይገባል። ለዚህ ደግሞ መላመድን የሚደግፉ ፋይናንስ ለማግኘት የሚረዱ መመሪያዎች ይበልጥ የተፍታቱ መሆን ይኖርባቸዋል ሲሉ ቪቶሪኖ ይሞግታሉ። ከ 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በተጓዳኝ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ (High-Level Forum) ላይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በሻርም ኤል ሼክ በተካሄደው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መላመድን፣ መከላከልን እና ዝግጁነትን ለማሻሻል ዓለም አቀፍ ትብብር ማጎልበት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አውስተዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥን አስመልክቶ ያወጣቸው የስምምነት ማዕቀፎች (United Nations Framework Convention on Climate Change (UNFCCC)) በርካታ ዝርዝርና ሚዛናዊ አካሄዶችን የያዙ ናቸው። ያም ሆኖ አተገባበራቸው እዚህ ግባ የማይባል በመሆኑ የሚታሰበውን ያህል ለውጥ ማምጣት ሳይችል ቀርቷል። በዚህም ቦረና ዞንን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የአየር ንብረት መዛባት፣ የሙቀትና የባህር ጠለል መጨመር፣ ጎርፍ፣ ድርቅ እንዲሁም ያልተገመቱ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ዓይነተኛ አማራጭ እንደሆነ ብዙዎቹ ይስማሙበታል። ዳሩ ግን አገራትን፣ አህጉርን፣ ዓለምን እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ግዙፍ ኩባንያዎችን ያስተሳስራል የተባለለት የአየር ንብረት ፋይናንስ በቅጡ ገቢራዊ ማድረግ ባለመቻሉ የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በርካታ ህዝቦች ዳፋውን ለመጋፈጥ ተገደዋል። የአየር ንብረት ፋይናንስን በመተግበር በመስኩ የተጎጂዎችን ቁጥር ሊቀንሱና የዓለምን ሥነ-ምህዳር ከተቻለ ወደ ቀድሞው ሊመልሱ አሊያም አሁን ባለበት አረጋግተው ሊያቆዩ የሚያስችሉ በርካታ አማራጮች ተግባራዊ ሊደረጉ ይገባል። ለአብነትም ለድሃ ሃገራት አርሶ አደሮች የግብርና ምርቶች ተገቢውን ዋጋ በመክፈል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን እንዲቋቋሙ ማድረግ ከአማራጮቹ መካከል አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግዙፎቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሚያስወግዷቸው በካይ ጋዞች ተመጣጣኝ የጤና ሥርዓት በመዘርጋት የታዳጊ ሃገራት ዜጎችን የጤና አገልግሎት ማሻሻል ሌላው አማራጭ ነው። የተፈጥሮ ኃብቶችን የሚጎዱ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ተፈጥሮን በሚንከባከቡ ዘዴዎች መተካት እንዲሁም ብክለትን የሚያስቀሩ የምርት ሂደቶች መለማመድ ጥቂቶቹ የመፍትሄ አማራጮች ተደረገው የሚወሰዱ ናቸው። በፓሪስ ከተደረሰውን የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ቀደም ብሎ በፈረንጆቹ 1994 ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም (Global Environment Facility-GEF) COP-16 ዓለም አቀፍ ጉባዔ በኋላ በ2010 አረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ (Green Climate Fund-GCF) እንዲሁም በ2001 ደግሞ ልዩ የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ (Special Climate Change Fund-SCCF) እና የመላመድ ፈንድ (Adaptation Fund-AF) የተባሉ ማዕቀፎች የተዘጋጁ ቢሆንም ስለጉዳዩ የሚያስረዱ ተከታታይ ስብሰባዎች ከማዘጋጀት በዘለለ ብዙ ርቀት መጓዝ ሳይችሉ ቀርተዋል። በቅርቡ በአለም ባንክ አሰባሳቢነት በኬንያ ናይሮቢ ተዘጋጅቶ በነበረው የአህጉሪቱን መሪዎች ባለሃብቶችንና ምሁራንን ባካተተውና “One Planet Summit” በተሰኘ መሰል ጉባዔ ላይም አፍሪካውያን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚገጥማቸውን ችግሮች ተከላክለው ሁለንተናዊ ዕድገታቸውን እንዲያፋጥኑ ካስፈለገ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምጣኔ ኃብት ፖሊሲ አዘጋጅተው መተግበር እንደሚኖርባቸው መግባባት ላይ የተደረሰ ቢሆንም አሁንም ጥያቄ ያስነሳው አፈጻጸሙ ስለመሆኑ ብዙ ተብሎለታል። ክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ የተባለ ድርጅት ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያመለክተው አፍሪካ እንደ ፈረንጆቹ የጊዜ ቀመር ከ 2020 እስከ 2030 ባሉት አሥር ዓመታት 2 ነጥብ 8 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር አሊያም በየዓመቱ ከ2 መቶ ሃምሳ ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያስፈልጋት ሲሆን አህጉሪቱ ከዘርፉ እያገኘችው ያለው ገንዘብም ከሚያስፈልጋት 12 በመቶውን ወይም 30 ቢሊየን ዶላር ብቻ ስለመሆኑ አስነብቧል። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው ሊሰሩ የሚችሉ በርካታ ተግባራት እንዳሏት የሚያትተው ሪፖርቱ ከአየር ንብረት ፋይናንስ የሚገኘው ገንዘብ በትራንስፖርት፣ በኃይል ልማት፣ በኢንዱስትሪ ብሎም በግብርና፣ በአፈርና በደን ኃብት አጠቃቀም ውጤታማ በሆነ መንገድ ከዋለ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ኃብቶች መንከባከብ ከማስቻሉም ባለፈ ላቅ ያለ ፋይዳ ይኖራዋል ብሏል። ይህ ሲሆን የሥራ ዕድል በመፍጠር የሥራ አጥ ቁጥርን በመቀነስ ለአህጉሪቱ ሰላምና መረጋጋት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖው ያስረዳል። ላለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ገቢራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራን የማስፋፋትና የተጎዱ አካባቢዎችን የማከም ሥራ እንዲሁም አይቀሬ የሆኑትን ከተሜነትና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ታሳቢ ያደረጉ የአየር ንብረት ፖሊሲዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ለአፍሪካ ሃገራት እየፈጠረው ያለው በጎ ተጽዕኖ በግልጽ እየታየ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ጥረት ግን በአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲደገፍ አገራዊና የተቀናጀ አሕጉራዊ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል። ከአጠቃላይ የአፍሪካ አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ግብጽ ብቻ 151 ቢሊየን ዶላር ከአየር ንብረት ንብረት ፋይናንስ ማግኘት እንደሚኖርባቸው የክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ ሪፖርቱ ይገልጻል። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በመጭው የCOP-28 ጉባዔ የራሷንና የአፍሪካን ፍላጎት የሚያስጠብቁ የፋይናንስ ትልሞችን የመንደፍ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባታል፡፡ የ COP-27 ጉባዔ ለአፍሪካ ያስገኘውን ውጤት እና አንድምታ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የመሪዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ እና አስተባባሪ በሆኑት በኬንያው ፕሬዝዳንት ሰብሳቢነት በኅብረቱ የአዲስ አበባ ጉባዔ ላይ በጥልቀት ይገመግማል ተብሎ ይጠበቃል። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ ጥረቷን የሚያጎለብት የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ጠንካራ ተሳትፎ ልታደርግ ይገባል። የአፍሪካ አገራት ገፍተው ረጅም ርቀት ያልሄዱበት የአየር ንብረት ፋይናንስ እና ሌሎች የድጋፍ አማራጮችን በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት በመጠቀም የአየር ንብረት ተጽዕኖን የሚቋቋሙበት ጠንካራ አቅም ሊገነቡ ግድ ይላቸዋል። በእርግጥም አፍሪካውያን መሪዎች በሚያደርጉዋቸው ስብሰባዎች በየማዕዝናቱ በድርቅ ሳቢያ ለምግብ እጦት የተዳረጉ ህዝቦቻቸውን የሚታደጉበት ሁነኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበትን ዘዴ ነድፈው ረጅም ርቀት ሊጓዙ ይገባል። ”
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 2728
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 1643
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 2474
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 1714
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል።   “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል።   ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 1890
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
በብዛት የታዩ
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 4067
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 3692
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 3167
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
የአገሪቷ ዓለም አቀፍ ውክልና እንዲጎላ እየተሰራ ነው-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
May 17, 2018 2851
አዲስ አበባ ግንቦት 9/2010 ኢትዮጵያ አሁን በዓለም ካላት የፖለቲካና ዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ እንዲሁም ተሰሚነትና ተደማጭነት ረገድ ያላትን ውክልና ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥቷል። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ መለሰ ዓለም በዚሁ ወቅት እንደተናሩት በሁለተኛው እድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ እንዲከፈቱ ከተያዙ ሚሲዮኖች መካከል በሞሮኮ፣ በአልጄርያና በሩዋንዳ ኤምባሲዎችን፤ እንዲሁም በቱሪክ ኢስታምቡል ቆንስላ ጄነራል መክፈት ተችሏል። በቀጣይ  በርካታ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችን በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በእስያና ኦሺኒያ እንዲሁም በመካክለኛው ምስራቅ አገራት ለመክፈት መታቀዱንም ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል። ይህም ውክልናን ለማስፋት፣ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ለማሳደግ፣ የዜጎችን መብት ለማስከበር፣ የኢንቨስትመንት፣ የቱሪዝም፣ የገጽታ ግንባታ እንዲሁም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ነው የጠቀሱት፡፡ በኢህአዴግ በኩል የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችም ለአገሪቱ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መዳበር የጎላ ሚና እንደሚኖራቸው አቶ መለሰ አብራርተዋል። የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ወገኖች በቅርቡ በአዲስ አበባ የተፈራረሙት የሰላም ስምምነት ማሳለጫ መድረክ እንዲተገበር ኢጋድና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግፊቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በመግለጫው ተጠቁሟል። ለሰላም ስምምነቱ መተግበር በዋና ዋና ተቀናቃኞች በኩል ቁርጠኝነት መኖሩን የገለጹት አቶ መለስ አንዳንድ ቦታዎች የሚታዩ ውጥረቶች ተፈተው ተግባራዊነቱ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
በብዛት የታዩ
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 4067
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 3692
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 3167
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
የአገሪቷ ዓለም አቀፍ ውክልና እንዲጎላ እየተሰራ ነው-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
May 17, 2018 2851
አዲስ አበባ ግንቦት 9/2010 ኢትዮጵያ አሁን በዓለም ካላት የፖለቲካና ዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ እንዲሁም ተሰሚነትና ተደማጭነት ረገድ ያላትን ውክልና ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥቷል። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ መለሰ ዓለም በዚሁ ወቅት እንደተናሩት በሁለተኛው እድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ እንዲከፈቱ ከተያዙ ሚሲዮኖች መካከል በሞሮኮ፣ በአልጄርያና በሩዋንዳ ኤምባሲዎችን፤ እንዲሁም በቱሪክ ኢስታምቡል ቆንስላ ጄነራል መክፈት ተችሏል። በቀጣይ  በርካታ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችን በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በእስያና ኦሺኒያ እንዲሁም በመካክለኛው ምስራቅ አገራት ለመክፈት መታቀዱንም ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል። ይህም ውክልናን ለማስፋት፣ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ለማሳደግ፣ የዜጎችን መብት ለማስከበር፣ የኢንቨስትመንት፣ የቱሪዝም፣ የገጽታ ግንባታ እንዲሁም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ነው የጠቀሱት፡፡ በኢህአዴግ በኩል የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችም ለአገሪቱ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መዳበር የጎላ ሚና እንደሚኖራቸው አቶ መለሰ አብራርተዋል። የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ወገኖች በቅርቡ በአዲስ አበባ የተፈራረሙት የሰላም ስምምነት ማሳለጫ መድረክ እንዲተገበር ኢጋድና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግፊቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በመግለጫው ተጠቁሟል። ለሰላም ስምምነቱ መተግበር በዋና ዋና ተቀናቃኞች በኩል ቁርጠኝነት መኖሩን የገለጹት አቶ መለስ አንዳንድ ቦታዎች የሚታዩ ውጥረቶች ተፈተው ተግባራዊነቱ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 2728
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ
Feb 12, 2023 2624
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 5/2015 በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸናፊ ሆነዋል። ዛሬ ማለዳ በተደረገው ውድድር በወንዶች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1 እስከ 10 እንዲሁም በሴቶች ከ1 እስከ 8 በመውጣት ፍጹም የበላይነትን ይዘዋል። በወንዶች አትሌት አብዲሳ ቶላ 2 ሰዓት ከ5 ደቂቃ ከ42 ሴኮንድ ውድድሩን በመጨረስ አሸንፏል። አትሌት አብዲሳ በአሜሪካ ኦሬጎን በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በተካሄደው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በወንዶች ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ ታናሽ ወንድም ነው። አትሌት ደሬሳ ገለታ እና አትሌት ሃይማኖት አለው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ይዘዋል። በሴቶች አትሌት ደራ ዲዳ 2 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ11 ሴኮንድ በመግባት የውድድሩ አሸናፊ ሆናለች። አትሌት ደራ የአትሌት ታምራት ቶላ ባለቤት ነች።አትሌት ሩቲ አጋ እና አትሌት ስራነሽ ይርጋ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል። በሁለቱም ጾታዎች ያሸነፉት አትሌቶች በተመሳሳይ የ80 ሺህ ዶላር ሽልማት ያገኛሉ። በተያያዘ ዜና ዛሬ ማለዳ በተካሄደው የሆንግ ኮንግ ማራቶን በሴቶች አትሌት ፋንቱ ኢቲቻ 2 ሰዓት ከ27 ደቂቃ ከ51 ሴኮንድ በመግባት አሸንፋለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ አትሌት ስንቄ ደሴ ሁለተኛ ወጥታለች።በወንዶች ኬንያዊው አትሌት ፊልሞን ኪፕቶ ኪፕቹምባ አሸንፏል። ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች ልመንህ ጌታቸው እና ሰንበታ ገዛ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 2474
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በድሬዳዋ በዕቅድ ዘመኑ ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተጠቆመ
May 24, 2018 2406
ድሬዳዋ ግንቦት 16/2010 በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዓመታት በተከናወኑ ተግባራት የገጠሩ ሕብረተሰብ በኢኮኖሚና በማህበራዊ አገልግሎቶች  ተጠቃሚ ቢሆንም ወጣቶችን የሥራ ዕድል ባለቤት ከማድረግ አንጻር ውስንነት መኖሩን የድሬዳዋ አስተዳደር ገጠር ነዋሪዎች ተናገሩ። በዕቅዱ የሁለት ዓመት ተኩል አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ  ውይይት ሲደረግ ነዋሪዎቹ እንዳሉት ለወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል የጎላ ክፍተት በመኖሩ የተቀናጀ ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል። በአስተዳደሩ የዋሂል የገጠር ቀበሌ ነዋሪ አቶ አህመድ መሀመድ እንዳሉት ባለፉት ሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ የገጠሩ ሕብረተሰብ በአካባቢው የትምህርት፣ የጤናና የመንገድ አገልግሎት በማግኘቱ ተጠቃሚ ሆኗል። የመስኖ ልማት ተደራሽነት እያደገ በመሆኑም በአካባቢያቸው የተወሰኑ ሰዎች የልማቱ ተጠቃሚ በመሆን ገቢያቸውን በማሳደግ ላይ መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡ በአሁኑ ወቅትም የመንገድ ውስኑነት መኖሩን የገለጹት አቶ አህመድ፣ በአካባቢው ለወጣቱ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግሮችን ለመፍታት ተገቢ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ ጠይቀዋል። የለገኦዳ ገጠር ቀበሌ ነዋሪ አቶ መሐመድ አብዱላሂ በዕቅድ ዘመኑ የገጠሩን ሕብረተሰብ ለመለወጥ የተደረገው ጥረት አበረታች ቢሆንም በሪፖርት የቀረበውና በተጨባጭ መሬት ላይ የተሰራው አንደማይጣጣም ጠቁመዋል። ወጣት ዚያድ አደም በበኩሉ "ባለፉት ሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ የገጠሩን ወጣቶች የሥራ ዕድልና የተዘዋዋሪ ገንዘብ ብድር አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ የተደረጉ ጥረቶች በገጠር ካለው የሥራ አጥ ወጣቶች ቁጥር ብዛት አንጻር አነስተኛ ነው" ብሏል፡፡ ተደራጅተውና ሰልጥነው ወደሥራ ለመሰማራት በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙት በርካታ ወጣቶች ተገቢ ድጋፍ በማድረግ  ጥያቄዎቻቸውን በአግባቡ መመለስ እንደሚገባ አመልክቷል፡፡ በተመሳሳይ ዜና በሁለተኛው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የሁለት ዓመት አፈጻጸም ላይ የድሬደዋ ከተማ ሴቶችና ወጣቶች ተወያይተዋል። በእዚህ ወቅት ተሳታፊዎች እንደተናገሩት ለከተማ ሴቶችና ወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት የተከናወኑ ተግባራት አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል። ከተሳታፊዎቹ መካከል ወጣት አዲስ ዘመድሁን እንዳለው አምናና ዘንድሮ ለወጣቱ ብድርና ስልጠና በመስጠት ወደሥራ እንዲገባ መንግስት ያከናወናቸው ተግባራት በወጣቱ ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል፡፡ ይሁንና የገበያ ትስስር የመፍጠር፣ የመስሪያና የመሸጫ ቦታዎች የማመቻቸት ክፍተቶች ቢስተካከሉ በዕቅዱ የተቀመጡ ግቦችን በተሻለ ማሳካት እንደሚቻል አመልክቷል፡፡ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚደረጉ ድጋፎች የተሻሉ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ ወይዘሮ ከዲጃ አሊ የተባሉ የድሬደዋ ከተማ ነዋሪ ናቸው፡፡ "የሴቶች ማህበራዊ፣ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳካት ከተፈለገ መንግስት የሚያወጣቸው ዕቅዶችና መመሪያዎች በአግባቡ ያለመተግበር ክፍተቶችን ማረም ይገባል" ብለዋል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደርን የሁለተኛ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈጻጻም ሪፖርት ያቀረቡት የድሬዳዋ ፕላንና ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ ተሰማ ባለፉት ሁለት ዓመታት በአስተዳደሩ የግብርናው ዘርፍ  በ4 ነጥብ 5 በመቶ ማደጉን ገልጸዋል። በገጠርና በከተማ በመንገድ፣ በትምህርትና በጤና መስክ የተቀመጡትን ግቦች ለማሳካት የተከናወኑ ተግባራት በጥሩ አፈጻጻም ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል፡፡ የሴቶችንና የወጣቶችን ተሳተፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሥራዎች ቢሰሩም ከሚጠበቀው ግብ አንጻር በቂ ባለመሆኑ በቀጣይ የተቀናጀ ሥራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በአስተዳደሩ የሥራ አ ጥ ምጣኔ በ2007 ከነበረበት 32 በመቶ ወደ 15 ዝቅ ቢልም ከተቀመጠው 12 በመቶ አንጻር ሲታይ ተጨማሪ ጥረቶችን ማድረግ አሰፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በውይይት መደረኮቹ ላይ የተገኙት የኢፌድሪ የመገናኛና ኢንፎርሜሽንና ቴክሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሲሳይ ቶላ በበኩላቸው በመላው አገሪቱ በየደረጃው ከሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በዕቅዱ አፈጻጸም ላይ ውይይት እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። በውይይቱ ላይ ከሕብረተሰቡ የሚነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተቀምረው በቀጣይ ሁለት ዓመት ተኩል ዕቅዱን በተሻለ ለማስፈጸም ርብርብ ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ አቶ ሲሳይ እንዳሉት በዕቅዱ የሁለት ዓመት ተኩል አፈጻጸም በትምህርት፣ በጤና፣ በመሰረተ ልማት ዘርፎች ውጤታማ ሥራዎች ተሰርተዋል። በቀጣይ ቀሪ ዘመን ከፍተቶችን ከመድፈን ባለፈ በተለይ የግብርና ዘርፉን ምርታማነት የበለጠ በማሳደግና የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማስፋት ርብርብ ይደረጋል ብለዋል፡፡ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈጻጸም ላይ የሚካሄደው ውይይት በቀጣይም ከባለሃብቱና ከሲቪክ ማህበራት ጋር በተመሳሳይ ይካሄዳል፡፡
መጣጥፍ
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 2067
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ)
Jan 25, 2023 2200
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ) አየለ ያረጋል (ኢዜአ) መዳረሻዬ ሽሬ እንዳስላሴ ነው። ለዘገባ ሥራ ከባህርዳር- ጎንደር- ደባርቅ- ሸሬ መንገድ ከሚዲያ ባልደረቦች ጋር እየተጓዝኩ ነው። የጥምቀት ሙሽራዋ ጎንደር እየተኳኳለች ነበር። ደባርቅ ከመድረሴ በፊት ዳባት ትገኛለች-የደጃች አያሌው ብሩ ቁርቁር ከተማ። ደጃች አያሌው ትውልዳቸው በጌምድር ጋይንት ቢሆንም ግዛታቸውና ኑሯቸው ዳባት ነበር። ሞገደኛው ደጃዝማች አያሌው ብሩ በጎንደር ማኅበረሰብ ዘንድ ዝናቸው የናኘ ነው። ደጃዝማች አያሌው በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ (ከልጅ ኢያሱ እስከ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ-መንግሥት) ታሪካዊ ክንውኖች ጉልህ ተሳትፎ አላቸው። አንዷን ብቻ ልምዘዝ። ራስ ተፈሪ ‘ንጉሠ-ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ’ ደጃች አያሌው የቅርብ ዘመዳቸውን ራስ ጉግሳ ወሌ ብጡልን (የንግሥት ዘውዲቱን ባለቤት) ወግተው የጎንደር ግዛት ‘ራስ’ ተብለው ለመሾም ቃል ቢገባላቸውም፤ ተልዕኳቸውን ተወጥተው ቃሉ ባለመፈጸሙ ደጃዝማቹ ከአጼው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። በዚህም:- "አያሌው ሞኙ፣ ሰው አማኙ ሰው አማኙ፣ የአያል ጠመንጃ፣ ስሟን እንጃ ስሟን እንጃ…” በማለት የጎንደር አዝማሪ አዚሟል። ዛሬም ይህ ግጥም የብዙ ባህላዊ ዘፈኖች አዝማች ነው። ደጃች አያሌው ብሩ ደፋር ናቸው ይባላል። ከአጼ ኃይለሥላሴ ጋር ቢቀያየሙም በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ሲመጣ ቅድሚያ ለአገሬ ብለዋል። ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘው የዶክተር ሀራልድ ናይስተሮም (ትርጉም ገበየሁ ተፈሪ እና ደሳለኝ አለሙ) መጽሐፍ እንደተጠቀሰው ደጃች አያሌው “ንጉሡ እንደኛ ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ ግን የሁላችንም ናት" ብለው ጦራቸውን መርተው በሽሬ ግንባር ዘምተዋል። ጉዟችን ቀጥሏል። ደባትን እያለፍን ነው። ‘እንኳን ደህና መጡ፤ ወደ ጭና ታሪካዊቷ ሥፍራ’ የምትለዋን ታፔላን በስተግራ እያየን ወደ ደባርቅ ገሰገስን። የሰሜን ተራሮች የብርድ ወጨፎ ያረሰረሳትን ደባርቅን ከማለፋችን ሊማሊሞ ጠመዝማዛ ቁልቁለት ተቀበለን። አስፈሪ የሊማሊሞ መልክዓ ምድር የደጋው ሰሜን ውርጭ እና የተከዜ በርሃ ኬላ ነው። ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድህን “የሰማይ የምድሩ ኬላ፣ የየብስ የጠፈሩ ዋልታ አይበገር የዐለት ጣራ፣ አይመክተው መከታ ሊማ-ሊሞ አድማስ ሰበሩ፣ በጎማ ፈለግ ይፈታ? በትሬንታ እግር ይረታ?…” ብሎ የመኪና መንገድ ተገንብቶበት በማየቱ ግርምቱን የተቀኘለትም ለዚህ ይመስላል። ከሊማሊሞ ቁልቁለት በኋላ አዲ-አርቃይ፣ ዛሪማ፣ ማይፀብሪ እና ሌሎች የጠለምት ወረዳ ከተማዎችን አልፈን፤ የዋልድባ ረባዳማ አካባቢዎችን ተሻግረን ተከዜ ወንዝ ደረስን። የዚህን መንገድ እና ተከዜ ወንዝን ሳስብ የሀዲስ ዓለማየሁ ትዝታ አስተከዘኝ። የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ጦር የወገንን ጦር ፊት ለፊት መቋቋም ሲሳነው በሰው ልጆች ላይ ተደርጎ የማያውቅ መርዝ በጅምላ የፈጀበት አሳዛኝ ታሪክ ነበር። በተከዜ ወንዝ ውሃን በመመረዝ የወገን ጦር ያለቀበት ሥፍራ ነው። የተከዜ ሸለቆ በኢትዮጵያዊያን ደምና አጥንት ዋጋ የተከፈለበት ነው። ሀዲስ ዓለማየሁ በአንድ ዕለት የተመለከቱትን እንዲህ ጽፈውታል። “የተከዜ ውሀ እመሻገሪያው ላይ ሰፊና ፀጥ ያለ ነው። ታዲያ ያ ሰፊ ውሀ፤ ገና ከሩቅ ሲያዩት ቀይ ቀለም በከባዱ የተበጠበጠ ይመስላል። “ምን ነገር ነው፤ ምን ጉድ ነው?” እየተባባልን ቀረብ ስንል መሻገሪያው በቁሙም በወርዱም ከዳር እስከ ዳር ሬሳ ሞልቶበት የዚያ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው። የሰው ሬሳ፣ የፈረስ እና የበቅሎ ሬሳ፣ ያህያ ሬሳ፣ ያውሬ ሬሳ፥ ሬሳ ብቻ! እግር ከራስ ራስ ከእግር እየተመሰቃቀለ እየተደራረበ ሞልቶበት፥ የዚያ ሁሉ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው”። ይሉናል። ቀጥለውም “በእውነቱ እንዲህ ያለውን መሳሪያ ምንም ጠላት ቢሆን በሰው ላይ ለማዋል የሚጨክን ሰው፥ ሰብዓዊ ስሜት የሌለው፣ አለት ድንጋይ የተፈጠረበት መሆን አለበት፤ እንዲህ ያለውን መሳሪያ በሰው ላይ ማዋል ሰብዓዊ ህሊና ሊሸከመው የማይችል እጅግ ከባድ መሆኑን ዓለም ሁሉ ያወቀውና ያወገዘው በመሆኑ የኢጣሊያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ከማድረጉ በቀር “ሌላ መንግሥት በሌላ አገር ላይ አደረገ’ ሲባል ተሰምቶ የሚያውቅ አይመስለኝም” ብለዋል። ከተከዜ ባህር ማዶ ጉዞዬ ያገኘኋት ሌላዋ ታሪካዊ ሥፍራ እንዳባጉና ናት። እንዳባጉና የወገን ጦር ትልቅ ገድል የፈጸመበት ነው። ጀግኖች አባቶቻችን የጠላት ታንክ ሳያስፈራቸው የጠላት ጅምላ ጨራሽ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ተቋቁመው ጠላትን ድባቅ የመቱበት፤ ወደ አክሱም እንዲያፈገፍግ ያደረጉበት ሥፍራ ነው። “የጠላት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በጦር ሜዳው ትንንሽ ቦምቦች አውቶማቲክ ጠመንጃ ይተኩስ ነበር። አቢሲኒያኖች ደግሞ ከጠላት ጋር ግብግብ ገጥመው ጉዳይም አልሰጡትም ነበር…” ይላል ዶክተር ሀራልድ ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘ መጽሐፉ። ይህ አካባቢ በሀገር ፍቅር የነደዱ ኢትዮጵያዊያን ደም ያፈሰሱበት፣ አጥንት የከሰከሱበት፤ ለኢትዮጵያ መስዕዋትነት የከፈሉበት ነው። ይህ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ቀጣና ነው። ቀኑ ተገባዷል። ጉዟችን እንደቀጠለ ነው። እኔም የማሽላ ማሳዎችን ግራ ቀኝ እየተመለከትኩ ለዕለቱ መዳረሻችን ወደሆነችው ሽሬ ከተማ ገባን። ሽሬ በትግርኛ ‘ሽረ’ ሲሉት ይደመጣሉ። በእርግጥ ሽሬን ለመጀመሪያ ጊዜ መርገጤ ነው። ዕለቱም ጥር ሥላሴ ነው። ሽሬ በጥር ሥላሴ ትደምቃለች፤ ሙሉ ስሟም ሽረ እንዳስላሴ ነው። የሽሬ ሥላሴ ጠበል ሽሬ ደርሰን ማረፊያችንን ያዝን። ጊዜው በጣም አልመሸምና ከተማዋን በቀላሉ መቃኘት ይቻላል። ሽሬ ሰፊና ደማቅ የዞን ከተማ ናት። ከመካከላችን የአንደኛው ባለሙያ ቤተሰቦች ሽሬ ነበሩና አስጠሩን። ለሥላሴ ጠበል ግብዣ። ባል እና ሚስቱ ከልክ በላይ መስተንግዶ አደረጉልን። ‘ጠብ እርግፍ አድርገው አስተናገዱን’ ማለት ይቀላል። እንግዳ መቀበል ነባር ኢትዮጵያዊ እሴታችን ቢሆንም ጦርነት ውስጥ ለቆየ አካባቢ የተለየ መልክ ነበረው። እንግዳ አቀባበላቸው በእርግጥም የመሃል አገር ሰው የናፈቃቸው ይመስላል። የተትረፈረፈ እህልና ውሃ አቅርበው በ’ብሉልን፤ ጠጡልን’ ተማጽኗቸው የተነፋፈቀ ቤተ-ዘመድ ግብዣ አስመሰሉት። የሥላሴው ጠበል የሸሬ ጠላ ቀረበ። የሸሬ ጠላ ሳስታውስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ታወሱኝ። የወቅቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምሀሩ ፕሮፌሰር ሽብሩ በዘመነ ደርግ በዕድገት በሕብረት ዘመቻ ተማሪዎቻቸውን ይዘው ሽሬ ዘምተው ነበር። በወቅቱ ታዲያ የሸሬ ጠላ ፍቅር ይዟቸው በየጊዜው ሲኮመኩሙ የተመለከቱ ሰዎች ‘ፕሮፌሰሩ ከጠፉ የሚገኙት ጠላ ቤት ነው’ ሲባሉ እንደነበር ‘ከጉሬ ማርያም እስከ አዲስ አበባ’ በተሰኘው ግለ ታሪካቸው አስፍረዋል። ከግብዣ መልስ ከማረፊያ ሆቴል ላይ ሆኜ ከተማዋን ስቃኛት ከጦርነት ድባቴ የተላቀቀች ይመስላል። የአመሻሽ ሕዝቡ እንቅስቃሴም ሆነ እስከ ሌሊቱ አጋማሽ የሚሰሙ የመዝናኛ ቤቶች ሙዚቃዎች የከተማዋን አሁናዊ መልክ የገለጠልኝ ነበር። ንጋት ላይ በቁርስና ቡና ሰዓታት ከሰዎች ጋር መስተጋብሬ ጀመረ። በጦርነት አዙሪት የከረመችው ሽሬና አካባቢው ኑሮ እጅጉን የከበደ ነበር። መልከ-ብዙ ማህበራዊ ቀውሶች አስተናግደዋል። አሁናዊ ምላሻቸው “ተመስገን፤ ያ ሁሉ አለፈ” የሚል ነው። ገበያው ተረጋግቷል፤ ማህበራዊ ኑሮ ተመልሷል። ድህረ-ሰላም ስምምነት ለሽሬ ነዋሪዎች ሁለንተናዊ እፎይታን አንብሯል። ከቀናት በኋላ በአክሱም የታዘብኩትም እንዲህ ነው። ኑሮን ያቀለለው የተቋማት አገልግሎት ጅማሮ በመጀመሪያ ዘገባ ስራዬ መሰረተ ልማትን አገልግሎት ቃኘሁ። ባንክ፣ ቴሌ፣ ሆስፒታል… መሰሎቹን። ተጠቃሚዎችንም፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ስራ ሃላፊዎችንም አነጋገርሁ። ከሰላም ስምምነቱ ማግስት ጀመሮ ተቋማቱ ወደስራ መመለሳቸው ከሁለንተናዊ ችግር እንደታደጋቸው ያነሳሉ። በትራንስፖርት እየተንቀሳቀሱ፣ በኤሌክተሪክ ስራዎቻቸውን እየከወኑ ነው። ለሁለት ዓመታት የተቋረጠው አገልግሎት አቅርቦት እና የአገልግሎት ፈላጊዎች ፍላጎት ግን አሁንም ሙሉ በሙሉ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ የተጠቃሚዎችም፤ የአገልግሎት ሰጭዎችም ሀሳብ ነው። በሽሬ ስሁል ሆስፒታል የተመለከትኳቸው፤ ያነጋገርኳቸው፤ ከታዳጊዎች እስከ አዛውንት ዕድሜ ያሉ ህሙማን የሰላም አየር ማግኘታቸው የሕይወታቸው ዑደት እንዲቀጥል አድርጓል። ድንገተኛም ሆነ ነባር ህመም ያለባቸው ሰዎች በነጻ እየታከሙ ነው ያገኘኋቸው። ሰላም ከሌለ መታከም ቀርቶ በቅጡ ማስታመም፤ በወጉ መቀበርም እንደማይቻል ገልጸውልናል። የጤና፣ የባንክና የቴሌኮም አገልግሎት የግብዓት ክፍተቶች የማሟላት ሰራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም በፌዴራል ደረጃ በየተቋማቱ የተመደቡ አስተባባሪዎች አረጋግጠውልኛል። የጸጥታ አካሉና የህብረተሰቡ ትብብርም የሚያስቀና እንደሆነ ግለሰቦችም፤ የጸጥታ አካላትም ነግረውኛል። አክሱም ጺዮን ማርያም፣ ሽሬ ስላሴ ንግስ፣ የጥምቀት በዓላት ከሶስት ዓመታት በኋላ በአደባባይ ታቦት ወጥቶ ተከብሯል። የፌዴራል ፖሊስ ተወካዮችም ይህንኑ ነው ያረጋገጡልኝ። የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከከተማ ነዋሪዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት ቤተሰባዊ የሆኑ ይመስላል። እንቅስቃሴያቸውም የሰላማዊ ቀጠና መልክ ያለው ነው፤ ዩኒፎርም ከመልበሳቸው በስተቀር ጀሌያቸውን ይንቀሳቀሳሉ። ይህ ደግሞ መተማመን ከመፍጠር ባለፈ ጦርነት ውስጥ ለቆየ ማህበረሰብ ከስነ ልቦና ጫና እንዲላቀቅ አይነተኛ ሚና እንደላው ይሰማኛል። ኢ-መደበኛ የሽሬና አክሱም ወጎች ያረፍኩበት ሆቴል ባለቤት ‘አደይ’ ተግባቢ ናቸው። ደግ እናት ይመስላሉ። ከገባን ጀምሮ ‘ጠላ ተጎንጩ፤ ቡና ጠጡ’ ጭንቃቸው ነው። ሁለት ቀን ቡና አስፈልተውልናል፤ ጠላ አቅርበው ዘክረውናል። ይህ ሁሉ ሲሆንም ለከተማው እንግዳ መሆናችንን እንጂ ስለሙያችንም ሆነ ስለሌላ ማንነታችን አያውቁም ነበር። ብዙ መጨዋወትና ውሎ አዳር በኋላ ነው ጋዜጠኛ ስለመሆናችን ያወቁት። አደይ ተጨዋች ናቸው። አማርኛ ያዝ ቢያደርጋቸውም ጨዋታቸው ‘ኩርሽም’ ነው- ተሰምቶ የማይሰለች። በአጋጣሚ ‘ሰለክላካ’ ስለምትባለዋ ታሪካዊ ሥፍራ ጠይቄያቸው እያወጋን ነበር። ‘እንደእናንተ ወጣቶች ሳለን ‘ሰለክላካን ያላዬ ሸዋን ያመሰግናል’ ይባል ነበር። ታዲያ አንድ የሸዋ ሰው መጣና ሰለክላካን አየና ‘በቃ ይቺ ናት’ ሰለክላካ’ ብሎ ተገረመ” ብለው አሳቁን። (የፍቅር እስከ መቃብር መሪ ገጸ-ባህሪው ‘በዛብህ’ ወደ ዲማ ጊዮርጊስ ሄዶ ‘የዲማ መልኳ እና ዝናዋ’ ተጣርሶበት እንደተገረመበት ቅጽበት መሆኑ ነው)። አደይ የተጀመረው ሰላም ፍጹም ምሉዕ ሆኖ ወደ ቀደመ ኢትዮጵያዊ መልካችን የምንመለስበት ጊዜ እንዲመጣ ይሻሉ። ከጦር-ነት ወደ ሰላም-ነት! ቆንጂዬዋ ፊዮሪ የኮሌጅ ተማሪ ነበረች። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጀምሮ በኋላም በጦርነት ሳቢያ ትምህርቷን ካቆመች ሦስት ዓመታት ሆኗታል። ጦርነቱ ከቆመ በኋላ የጀበና ቡና ጀምራለች። ደንበኞቿ ሰብሰብ ብለን እንቀመጣለን። ፊዮሪ ከስኒ ማቅረቢያዋ ላይ አነስተኛ ጀበናዋን፤ የሚያማምሩ ስኒዎቿን እና መዓዛው ከሚያውድ የዕጣን ማጨሻዋ ጋር ሰድራ ይዛ ትቀርባለች። ከመካከላችን ካለው ጠረጴዛ ላይ ታስቀምጥና እርሷም ወንበር ይዛ ከመካከላችን ትቀመጣለች። ቡናው እስኪሰክን ጨዋታዋን ታስኮመኩመናለች። ቡናው ከሰከነ በኋላ ቡናዋን ቀድታ ለእያንዳንዳችን በእጃችን እያነሳች ትሰጣለች። በሽሬ ቡና የሚቀርበው በዚህ መልክ ነው። ለፊዮሪ እና መሰሎቿ ጦርነቱ ክፉ ጠባሳ መጣሉ፤ ተስፋቸው ላይ መጥፎ አሻራ ማስቀመጡን ታነሳለች። አሁን ግን ብሩህ ተስፋ ሰንቃለች። ስለነገዋም “ሰላሙ ይዝለቅልን፤ ትምህርቴን ለመቀጠል እመኛለሁ” ትላለች። አክሱም ከሽሬ በስተሰሜን 60 ኪሎ ሜትር ይርቃል። ከሽሬ አክሱም ስንንቀሳቀስ ከጥምቀት ዕለት በስተቀር ገበሬው የግብርና ሥራዎቹን እየከወነ ነበር። አርሶ አደሩ ያርሳል፤ መስኖውን ያለማል። የተዘራውን ውሃ ያጠጣል። የበቀለ ቡቃያውን ይኮተኩታል። ከጦርነት ወደ ልማት መዞሩን ዐይኔ ታዝቧል። በጥምቀት ዋዜማ፤ የከተራ በዓል ዕለት ሁለት ጎራማይሌ የረፋድ ትዕይንቶችን ላንሳ። ከአክሱም ከተማ ወደ አድዋ እና ሽሬ መገንጠያ አካባቢ ሰፊ የቀንድ ከብት ገበያ ነበር። እውነተኛ የዓመት በዓል ገበያ መልክ ያለው ትዕይንት ነበር። በተለይም የፍየል ዋጋ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተገበያዩ እንደነበር ሰምቻለሁ። ታሪካዊቷን አክሱም ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ የረገጥኳት/የተሳለምኳት ከአራት ዓመት በፊት በ2011 ዓ.ም ይመስለኛል። ከገበያው ቀጥሎ በታቦተ-ጽዮን መገኛዋ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ደጅ፣ በጥንታዊያኑ የአክሱም ሐውልት መገኛ አደባባይ ነበር። ከጽዮን በስተምዕራብ በአርባቱ እንሰሳ በኩል፤ በቅዱስ ያሬድ ዋርካ… አድርጌ በጽዮን ዋናው በር ደረስኩ። ማራኪ የአክሱም የኮብልስቶን መንገዶች ኦና ናቸው። የወትሮው ግርግር ናፍቋቸዋል። ከጽዮን ቅጥር ግቢ በዋናው በር በስተውጭ አነስተኛ እና ብቸኛ ዋንዛ በኮብልስቶን መሃል ነበረች። ዛሬም ለምልማ አለች። በዚህ አካባቢ ድሮ የነጭ ጎብኚ ጋጋታ፣ የጽዮን ደጅ ጠኚ ምዕመን… የተጨናነቀ ነበር። እንደ ድሮው የፎቶ አንሺ ግርግር፣ የአክሱም መስቀል ቀርጸው የሚሸጡ ወጣቶች ጫጫታ የለም። ይልቁንም እርጥባን የሚሹ አቅመ ደካሞችና ህፃናት ነበሩ። ጦርነት የሥፍራዋን መልክ አጠይሞታል። ያም ሆኖ ከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ሙሉ በኩሉሄ ባይባልም ወደነበረበት እየተመለሰ ነው። የግልም ሆነ የመንግሥት ባንኰች ሥራ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከአክሱም ሐውልት ወደ ሌላ ሰፈር አቀናሁ። ትርሐስ ገና ታዳጊ ልጅ ነች። ጠይም፤ ስርጉድ፣ ሳቂታና ተረበኛ አይነት ልጅ ነች። እንደ ሽሬዋ ፊዮሪ መንገድ ዳር የጀበና ቡና እየሰራች ነው። ከሩቅ የመጣን እንግዶች መሆናችንን ስታውቅ፤ ደስታዋ ከገጿ ይነበብ ነበር። ያለፉ ጊዜያትን ሰቆቃ አጫወተችን። ስለቀጣይ ዕጣ ፈንታዋ እና ዕቅዷ ስታወራ ትቆይና “የሰው ልጅ ግን በጣም ከሃዲ ነው። ከወራት በፊትኮ ስለቢዝነስ አላስብም ነበር። መቼ እሞታለሁ እንጂ” ብላ ራሷን ትወቅሳለች። ወደ ሰማይ አንጋጣ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች። ጦርነት ተራውንም ሕዝብ ለመልከ-ብዙ ቀውስ ዳርጎት እንደቆየ ታነሳለች። ዛሬ ሁሉ አልፎ ሰላም መውረዱ ለመጨዋወት መብቃቷ ለእርሷ ትልቅ ብሥራት ነው። ይህ ለትርሐስ ብቻ ሳይሆን ለመላው አክሱማዊያን መሆኑ እሙን ነው። አክሱም ከተማ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ከዋለችበት ጊዜ ጀምሮ በከተማዋ በሻለቃ አዛዥነት የተሰማራ የፌደራል ፖሊስ አባልም ያጋጠመውን አሳዛኝ ገጠመኞች አጫውቶኛል። ጦርነቱ ቢራዘም ኖሮ በተራው ሕዝብ ላይ ምን ያህል የከፋ ጉዳት ይደርስ እንደነበር በአሳዛኝ ሁኔታ ገልጾልኛል። አክሱሞች ያን ሁሉ አልፈው ሰላም አየር ነፍሶ፣ ከስጋት ቆፈን ተላቀው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ተመልሰዋል። የዛሬ ሳምንት ሰርክ(11 ሰዓት) ላይ አክሱም የከተራ በዓል በድምቀት አክብራለች። ታቦተ-ጽዮን ወደ ባህረ- ጥምቀቱ ስትወርድ፤ ወግና ሥርዓቱ ተጠብቆ፣ ሕዝቡ በሀበሻ ነጫጭ አልባሳት፣ ካህናት በልብሰ ተክህኖ ደምቀው … እየተከወነ ነበር። አንዲት እናት ለአማርኛ ተናጋሪ በቀረበ አነጋገር እያለቀሱ ታቦት እየሸኙ ነው። ትኩር ብዬ ሳያቸውም ዕንባቸው ዱብ ዱብ ይላል። “ከዚያ ሁሉ መከራ አልፎ ለዚህ በቃን፤ ተመስገን” እያሉ እልልታውን ያቀልጡታል። በደስታ እያነቡ ነበር። ይህ ስሜት የብዙኃኑ አክሱማዊያን እናቶች እንደሆነ መገመት ቀላል ነው። አክሱም በኮቪድ እና በኋላም በጦርነቱ ምክንያት ባህረ-ምቀት ታቦት ወጥቶ ሲከበር ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ከወትሮው በተለየ ድምቀትና ውበት በሰላምና በደስታ፤ በአደባባይ እልልታና ሆታ በማክበራቸው ልዩ ስሜት ፈጥሮባቸዋልና! እናም በአክሱም የከተራ ሆነ የበዓለ-ጥምቀት ክብረ-በዓላት በሰላም ስምምነቱ ማግስት በድምቀት ተከውኖ አለፈ። የሃይማኖት አባቶቹም ሆኑ ምዕመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅም የዘንድሮው ክብረ-በዓል ካለፉት ዓመታት ነባራዊ ሁኔታ ጋር እያነጻጸሩ፤ ትልቅ ብሥራትና መልክ እንዳለው ገልጸዋል። ሰላም እንዲጸና፤ ነባር ኢትዮጵያዊ አንድነትና መተባበር እንዲመለስ ጽኑ መሻታቸውን ነግረውናል። በበጎ ቀን የማውቃትን አክሱም፤ ከረዥም ጊዜ በኋላ አሁናዊ መልኳን ታዝቤ፤ የነገ ትዝታ ሰንቄ ተመለስኩ!! ሰላም ለኢትዮጵያ!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም