ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የበለፀገችና ህብረብሄራዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና መወጣት አለባቸው - ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር)
Nov 28, 2025 40
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ አንድነቷ የጸና የበለፀገችና ህብረብሄራዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ወጣቶች ውይይት ለሰላም ማህበር ጋር በመተባበር ወጣቶች ለሰላም ግንባታና ለማህበራዊ ትስስር መጠናከር በሚኖራቸው ሚና ላይ ያተኮረ "አዲስ ፎረም 2025" እየተካሄደ ይገኛል።   የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ወጣቶች ለሰላም፣ አንድነት፣ አብሮነት፣ ለሀገር ብልፅግና ወሳኝ ሚና አላቸው፡፡ መንግሥት አስቻይ ሁኔታዎችን በመፍጠር ወጣቶች ለሀገር ልማት የበኩላቸውን እንዲወጡ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። አንድነቷ የፀና፣ የበለፀገችና ህብረብሄራዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት ወጣቶች ያላቸውን አቅም በመጠቀም ሚናቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል፡፡ "የኢትዮጵያ ወጣቶች ለሰላምና ደህንነት ሀገራዊ የድርጊት መርሃግብር" መጠናቀቁን የገለጹት ሚኒስትሯ፤ ለገቢራዊነቱ የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶች እና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር ቀጀላ መርዳሳ በበኩላቸው፤ ወጣቶች ግንባር ቀደም የሰላም ዘብ የመሆን ሀገራዊ ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። ለዘላቂ ልማትና ኢኮኖሚያዊ እድገት የወጣቶች ሚና ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ ወጣቶች ልማት ላይ በስፋት እንዲሳተፉ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ለአመራርነት ለማብቃት በክህሎት ልማት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡   የኢትዮጵያ ወጣቶች ውይይት ለሰላም ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወጣት ኢንጂነር ጫላ አሰፋ፤ ሰላም እያንዳንዳችን የምንገነባው የጋራ ህንፃ መሆኑን ገልጿል። ሰላም የሁሉ ነገር መነሻና መሰረት፤ ለልማትና አንድነት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ ማህበሩ ወጣቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ መሀንዲስ፣ የለውጥ መሪ እንዲሆኑም ተናግሯል። የፎረሙ ተሳታፊ ወጣቶች በበኩላቸው ወጣቶች በሀገር ግንባታና ሰላም የላቀ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸው የሚናቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡
ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ዘላቂ ልማትን በማረጋገጥ ሂደት ወሳኝ ሚና ሊጫወቱ ይገባል -ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
Nov 28, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሀገራዊና አህጉራዊ ዘላቂ ልማትን በማረጋገጥ ሂደት ወሳኝ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ75ኛ ዓመት አልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል አካል የሆነ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አጋሮች መርሃ ግብር ተካሂዷል።   በመርኃ ግብሩ የትምህርት ሚኒስትርና የዩኒቨርሲቲው ቻንስለር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር)፣ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት አብረው የተጓዙ አጋሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በዚህም "ለዘላቂ ልማት እና ለአፍሪካ መጻኢ ዕጣ ፈንታ የከፍተኛ ትምህርት ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ለሀገራት ሁለንተናዊ እድገት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና ወሳኝ ነው። የተማረ የሰው ኃይልን በማፍራት እንዲሁም በጥናትና ምርምር ስራዎች ዘላቂ ልማትን የማረጋገጥ ሂደት ላይ አሻራቸውን ማሳረፍ ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።   የደቡብ ደቡብ ትብብር ምክትል ዋና ፀሐፊ ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም በበኩላቸው፤ ዘላቂ ልማት የሚለካው በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ብቻ ሳይሆን በእውቀትና በእሴት መጎልበት እንዲሁም በማህበረሰብ ለውጥ ጭምር መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዘላቂ ልማት መረጋገጥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያላቸው ሚና ቁልፍ መሆኑንም አስረድተዋል። በመድረኩ የፓናል ውይይት ተሳታፊ የሆኑት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዘላቂ ልማት ላይ ስርዓተ ትምህርት ቀርፀው መስራት እንዳለባቸው አመላክተዋል።   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ የድህረ ምረቃ ጥናትና ምርምር ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጽጌ ገብረማርያም፥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማህበረሰብ ተኮር ምርምር እና ፈጠራ ላይ የማተኮር ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት በጥናት ላይ የተመሠረተ የፖሊሲ አወጣጥ ላይ የሚያበረክቱት አስተዋፅዖ ወሳኝ እንደሆነ የተናገሩት ደግሞ የባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ ናቸው። በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች የሀገራዊ የፖሊሲ ውሳኔዎችን ለማዘጋጀት የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶችን ማፍለቅ እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የፍትህ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ሀገራዊ ሪፎርም አድርጋለች
Nov 28, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የፍትህ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ሀገራዊ ሪፎርም ማድረጓን የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) ገለጹ። የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ ከፍትሕ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ፈዴራል ጠበቆች ማህበር ጋር በመተባበር 30ኛ ዓመት የምሥረታና ዓመታዊ ጉባኤውን በአፍሪካ ሕብረት ማካሄድ ጀምሯል፡፡ የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በለውጡ ዓመታት ከሀገር አልፎ ቀጣናውን የሚያስተሳስሩ የዲሞክራሲ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ጥረት እያደረገች ነው።   በዚህም ባለፉት ዓመታት ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የፍትህ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ሀገራዊ ሪፎርም ማድረጓን ተናግረዋል። በፍትህ ዘርፉ የተደረገው ሪፎርም የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ህጋዊና ገለልተኛ ተቋም ሆኖ እንዲፈጠር አስችሏል ብለዋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ከአምስቱ የፍትህ ዘርፍ መሰረቶች አንዱ እንዲሆን መደረጉን ገልጸዋል። ይሄውም ኢትዮጵያ በሀገራዊ ሪፎርሙ የፍትህ ተቋማትን ለማጠናከር የወሰደችውን ወሳኝ እርምጃ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበርና የሌሎች የቀጣናው ሀገራት የፍትሕ ተቋማት ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው አንስተዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ጽህፈት ቤት ዋና ኃላፊ አምባሳደር ሞሐመድ ኤል አሚን ሱፍ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063ን ግብ ለማሳካት ያግዛል ብለዋል።   በአፍሪካ ሀገራት ወደ መድብለ ፓርቲ ስርዓት በሚያደርጉት ሽግግር የፖለቲካ መረጋጋትን ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት መልካም አስተዳደር ዲሞክራሲና ፍትሕን ለማስፈን የሚሰሩበት ጊዜ አሁን ነው ያሉት ሀላፊው፤ ሕብረቱ የተለያዩ የዲሞክራሲ ተቋማትን በማቋቋም ለፍትህ ስርዓት መስፈን አባል ሀገራትን እየደገፈ ነው ብለዋል። የአፍሪካ የዲሞክራሲ አስተዳደርና የምርጫ ቻርተር፣ የአፍሪካ ሰላምና ደህንነት አርክቴክቸር ግጭትን በመከላከል ሰላምን ማስፈን የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረት የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የያዛቸውን አጀንዳዎች ከግብ ለማድረስ የፍትሕ ተቋማትና የህግ ባለሙያዎች ለመልካም አስተዳደር መስፈንና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል፡፡ የሕብረቱ አባል ሀገራት የጋራ እሴቶቻቸውን በማጎልበት በትብብር መስራት እንዳለባቸው ገልጸው፤ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ወጣት የህግ ባለሙያዎችን በማሰልጠን ለህግ የበላይነትና መልካም አስተዳደር መስፈን ሚናውን መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡   የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ ፕሬዝዳንት ረመዳን አቡበከር፤ ተቋሙ በቀጣናው ፍትሕን በማረጋገጥ የህግ የበላይነት የማስፈን ኃላፊነት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ የሕግ የበላይነትና ዲሞክራሲ በራሱ የሚቀጥል ሳይሆን በየጊዜው ልምምድን የሚጠይቅ መሆኑን በማንሳት፤ የዲሞክራሲ ተቋማትን መገንባት ካልተቻለ አለመረጋጋት ይፈጠራል ብለዋል፡፡ የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ በሽዎች የሚቆጠሩ ወጣት የህግ ባለሙያዎችን በማሰልጠን ለአፍሪካ ሕብረት መልካም አስተዳደር፣ ሰብዓዊ መብትና ዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ግብ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቀጣናው በተከፋፈለ መንገድ ንግድና ኢንቨስትመንትን ማሳደግ እንደማይቻል ገልጸው፤ የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ በሀገራት መካከል የህግ ስርዓት ትብብር እንዲፈጠር ሚናውን ይወጣል ብለዋል፡፡ ከዚህ አንፃር የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር ኢትዮጵያ በፍትህ ተቋማትን ለማጠናከር የጀመረችውን እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ጌታቸው የምስራቅ አፍሪካ የህግ በማህበረሰብ የቀጣናው ስትራቴጂካዊ አጋር ሆኖ እንደሚቀጠል ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ዜጎችን የፍትሕ እጦት ለመፍታት፣ ለህግ የበላይነት መረጋገጥ ሚናውን ይወጣል ብለዋል፡፡ ከምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ጋር በትብብር በመስራት የቀጣናውን ንግድና ኢንቨስትመንት ለማሳለጥ አበክሮ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ለፍትህ ዘርፉ ዕድገት ገንቢ ሚና እንዳለው በማንሳት፤ ተቋሙን ለማጠናከር አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል ብለዋል፡፡      
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን አለባት-የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል
Nov 28, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ። ከቀናት በፊት በሁለትዮሽ ወታደራዊ ጉዳዮች ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጄነራል መኮንኖች ጋር የመከሩት ጄነራል ፒየር ሺል የተለያዩ ተቋማትን ከጎበኙ በኋላ ከጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋርም ተወያይተዋል።   "ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ ለማግኘት ያላትን ፍላጎት እንዴት ይመለከታሉ?" በሚል ከመከላከያ ሚዲያ ጋዜጠኞች ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል፤ "ኢትዮጵያ በጣም ትልቅ ሐገር ናት፣ በጣም ትልቅ የኢኮኖሚ ኃይልና ሕዝብም ያላት በመሆኑ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን አለባት ብለዋል። ከኢትዮጵያ ጋር የተካሄደው ወታደራዊ ትብብር ዋነኛ ዓላማም ፈረንሳይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ለማሻሻል አዲስ አበባ በመገኘቴ በጣም ኮርቻለሁ ብለዋል። ስለዚህ ትብብራችን በዋናነት የወታደራዊ ቁሳቁስ ድጋፍ ፣የሠላም ማስከበር ሥራዎች፣ የፈንጅ አወጋገድ ተግባራት ላይ፣ በሠው ኃይል ሥልጠና እና በሌሎችም ነው" ብለዋል። ጄነራል ፒየር ሺል ኢትዮጵያ የቀጠናውን ደኅንነት ለማስጠበቅ ዋነኛ ተዋናይ መሆኗን ገልፀው፣ የኢትዮጵያ ተሳትፎ እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና እንደ ፈረንሣይ ሠራዊት ተወካይ የኢትዮጵያን ሠራዊት እንደሚደግፉም አንስተዋል።   የኢትዮጵያን ሠራዊት ተሣትፎ በማድነቅ "ኢትዮጵያ በጣም ትልቅ ሐገር ናት፣ በጣም ጠንካራና ትልቅ ሠራዊትም አላት ከዚህ ሠራዊት ብዙ የምንማረው ነገር አለ ሲሉም አስረግጠው መናገራቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል። ከሰሞኑ በአዲስ አበባ የሚገኘው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዋናው መምሪያ የዓለም ኃያላንን ጨምሮ የተለያዩ ሐገራት የጦር መሪዎችን አስተናግዷል።
ትልልቅ የልማት አጀንዳዎችን ለማሳካት የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ የተግባቦት ሥራዎችን ማጠናከር ይገባል-ከፍተኛ አመራሮች
Nov 28, 2025 65
አዲስ አበባ፤ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ትልልቅ የልማት አጀንዳዎችን ለማሳካት የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ የተግባቦት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር አዘጋጅነት የፖለቲካ ትንተና፣ማህበራዊ ሚዲያና ሁኔታ ትንተና ላይ በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአሰልጣኞች ስልጠና መርሃ ግብር ተካሂዷል።   በሥልጠና መርሃ ግብሩ ላይ በፌደራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊዎችና የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትርና በብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል እንዳሉት፤ አመራሩ በሪፎርም ሥራዎች በመታገዝ ትልልቅ የልማት ግቦችን ለማሳካት እየተጋ ነው። እነዚህ የልማት ግቦች የሚሳኩት በሕዝቡና በመንግሥት መካከል መሰናሰል ሲፈጠር ነው ያሉት አቶ መላኩ፥ ህብረተሰቡን በልማት አጀንዳዎች ላይ በተሻለ መልኩ የሚያሳተፉ የተግባቦት ሥራዎችን በትኩረት ማከናወን ይገባል ብለዋል። አመራሩ እየተለዋወጠ ባለው የዓለም ሁኔታ ያሉ ዕድሎችን ለመጠቀም ወቅቱን የዋጀ እውቀት በመጨበጥ ህዝቡን በውጤታማነት የማሳተፍ ሥራን ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። ሥልጠናው በመረጃ ላይ በመመስረት ከሕዝቡ ጋር ይበልጥ ተናቦ ለመስራት ምቹ አውድ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።   የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙሳ አህመድ በበኩላቸው፥ በመደመር መንግሥት እይታ ፈጣንና ፈጠራ የታከለበት አገራዊ አድገት ለማረጋገጥ ግብ ተይዞ ወደ ሥራ ተገብቷል። ግቡን በውጤታማነት ለማጠናቀቅ በየጊዜው የፖለቲካ ትንተና ላይ የተመሰረቱ እርምጃዎች መውሰድ እንደሚገባ ጠቁመው፥ ለዚህም አመራሩ ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንዳለበት አመልክተዋል። የብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ መሀመድ እድሪስ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የኢኮኖሚ አመራሩ አካታች ኢኮኖሚ ግንባታ፣ ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና መሰል ጉዳዮች ላይ አጀንዳ ቀርጾ መሥራት ይጠበቅበታል።   የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የከተሞች ፎረምን ጨምሮ ሕዝቡን በማሳተፍ በውጤታማነት እየተተገበሩ ያሉ አጀንዳዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ መሰል ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። አመራሩ ፖሊሲዎችን ወደ አጀንዳነት መቀየር ላይ በሰፊው ሊሰራበት የሚገባው ጉዳይ ነው ብለዋል።   በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የብልፅግና ስትራቴጂ ጉዳይ ዋና ዳይሬክተር ተተካ በቀለ በበኩላቸው፤ የድህረ እውነት ፈተናዎች የሆኑትን ሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን መታገል ላይ አመራሩ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የሚታይ
ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ዘላቂ ልማትን በማረጋገጥ ሂደት ወሳኝ ሚና ሊጫወቱ ይገባል -ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
Nov 28, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሀገራዊና አህጉራዊ ዘላቂ ልማትን በማረጋገጥ ሂደት ወሳኝ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ75ኛ ዓመት አልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል አካል የሆነ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አጋሮች መርሃ ግብር ተካሂዷል።   በመርኃ ግብሩ የትምህርት ሚኒስትርና የዩኒቨርሲቲው ቻንስለር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር)፣ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት አብረው የተጓዙ አጋሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በዚህም "ለዘላቂ ልማት እና ለአፍሪካ መጻኢ ዕጣ ፈንታ የከፍተኛ ትምህርት ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ለሀገራት ሁለንተናዊ እድገት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና ወሳኝ ነው። የተማረ የሰው ኃይልን በማፍራት እንዲሁም በጥናትና ምርምር ስራዎች ዘላቂ ልማትን የማረጋገጥ ሂደት ላይ አሻራቸውን ማሳረፍ ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።   የደቡብ ደቡብ ትብብር ምክትል ዋና ፀሐፊ ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም በበኩላቸው፤ ዘላቂ ልማት የሚለካው በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ብቻ ሳይሆን በእውቀትና በእሴት መጎልበት እንዲሁም በማህበረሰብ ለውጥ ጭምር መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዘላቂ ልማት መረጋገጥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያላቸው ሚና ቁልፍ መሆኑንም አስረድተዋል። በመድረኩ የፓናል ውይይት ተሳታፊ የሆኑት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዘላቂ ልማት ላይ ስርዓተ ትምህርት ቀርፀው መስራት እንዳለባቸው አመላክተዋል።   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ የድህረ ምረቃ ጥናትና ምርምር ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጽጌ ገብረማርያም፥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማህበረሰብ ተኮር ምርምር እና ፈጠራ ላይ የማተኮር ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት በጥናት ላይ የተመሠረተ የፖሊሲ አወጣጥ ላይ የሚያበረክቱት አስተዋፅዖ ወሳኝ እንደሆነ የተናገሩት ደግሞ የባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ ናቸው። በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች የሀገራዊ የፖሊሲ ውሳኔዎችን ለማዘጋጀት የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶችን ማፍለቅ እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የፍትህ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ሀገራዊ ሪፎርም አድርጋለች
Nov 28, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የፍትህ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ሀገራዊ ሪፎርም ማድረጓን የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) ገለጹ። የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ ከፍትሕ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ፈዴራል ጠበቆች ማህበር ጋር በመተባበር 30ኛ ዓመት የምሥረታና ዓመታዊ ጉባኤውን በአፍሪካ ሕብረት ማካሄድ ጀምሯል፡፡ የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በለውጡ ዓመታት ከሀገር አልፎ ቀጣናውን የሚያስተሳስሩ የዲሞክራሲ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ጥረት እያደረገች ነው።   በዚህም ባለፉት ዓመታት ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የፍትህ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ሀገራዊ ሪፎርም ማድረጓን ተናግረዋል። በፍትህ ዘርፉ የተደረገው ሪፎርም የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ህጋዊና ገለልተኛ ተቋም ሆኖ እንዲፈጠር አስችሏል ብለዋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ከአምስቱ የፍትህ ዘርፍ መሰረቶች አንዱ እንዲሆን መደረጉን ገልጸዋል። ይሄውም ኢትዮጵያ በሀገራዊ ሪፎርሙ የፍትህ ተቋማትን ለማጠናከር የወሰደችውን ወሳኝ እርምጃ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበርና የሌሎች የቀጣናው ሀገራት የፍትሕ ተቋማት ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው አንስተዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ጽህፈት ቤት ዋና ኃላፊ አምባሳደር ሞሐመድ ኤል አሚን ሱፍ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063ን ግብ ለማሳካት ያግዛል ብለዋል።   በአፍሪካ ሀገራት ወደ መድብለ ፓርቲ ስርዓት በሚያደርጉት ሽግግር የፖለቲካ መረጋጋትን ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት መልካም አስተዳደር ዲሞክራሲና ፍትሕን ለማስፈን የሚሰሩበት ጊዜ አሁን ነው ያሉት ሀላፊው፤ ሕብረቱ የተለያዩ የዲሞክራሲ ተቋማትን በማቋቋም ለፍትህ ስርዓት መስፈን አባል ሀገራትን እየደገፈ ነው ብለዋል። የአፍሪካ የዲሞክራሲ አስተዳደርና የምርጫ ቻርተር፣ የአፍሪካ ሰላምና ደህንነት አርክቴክቸር ግጭትን በመከላከል ሰላምን ማስፈን የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረት የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የያዛቸውን አጀንዳዎች ከግብ ለማድረስ የፍትሕ ተቋማትና የህግ ባለሙያዎች ለመልካም አስተዳደር መስፈንና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል፡፡ የሕብረቱ አባል ሀገራት የጋራ እሴቶቻቸውን በማጎልበት በትብብር መስራት እንዳለባቸው ገልጸው፤ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ወጣት የህግ ባለሙያዎችን በማሰልጠን ለህግ የበላይነትና መልካም አስተዳደር መስፈን ሚናውን መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡   የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ ፕሬዝዳንት ረመዳን አቡበከር፤ ተቋሙ በቀጣናው ፍትሕን በማረጋገጥ የህግ የበላይነት የማስፈን ኃላፊነት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ የሕግ የበላይነትና ዲሞክራሲ በራሱ የሚቀጥል ሳይሆን በየጊዜው ልምምድን የሚጠይቅ መሆኑን በማንሳት፤ የዲሞክራሲ ተቋማትን መገንባት ካልተቻለ አለመረጋጋት ይፈጠራል ብለዋል፡፡ የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ በሽዎች የሚቆጠሩ ወጣት የህግ ባለሙያዎችን በማሰልጠን ለአፍሪካ ሕብረት መልካም አስተዳደር፣ ሰብዓዊ መብትና ዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ግብ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቀጣናው በተከፋፈለ መንገድ ንግድና ኢንቨስትመንትን ማሳደግ እንደማይቻል ገልጸው፤ የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ በሀገራት መካከል የህግ ስርዓት ትብብር እንዲፈጠር ሚናውን ይወጣል ብለዋል፡፡ ከዚህ አንፃር የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር ኢትዮጵያ በፍትህ ተቋማትን ለማጠናከር የጀመረችውን እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ጌታቸው የምስራቅ አፍሪካ የህግ በማህበረሰብ የቀጣናው ስትራቴጂካዊ አጋር ሆኖ እንደሚቀጠል ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ዜጎችን የፍትሕ እጦት ለመፍታት፣ ለህግ የበላይነት መረጋገጥ ሚናውን ይወጣል ብለዋል፡፡ ከምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ጋር በትብብር በመስራት የቀጣናውን ንግድና ኢንቨስትመንት ለማሳለጥ አበክሮ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ለፍትህ ዘርፉ ዕድገት ገንቢ ሚና እንዳለው በማንሳት፤ ተቋሙን ለማጠናከር አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል ብለዋል፡፡      
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን አለባት-የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል
Nov 28, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ። ከቀናት በፊት በሁለትዮሽ ወታደራዊ ጉዳዮች ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጄነራል መኮንኖች ጋር የመከሩት ጄነራል ፒየር ሺል የተለያዩ ተቋማትን ከጎበኙ በኋላ ከጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋርም ተወያይተዋል።   "ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ ለማግኘት ያላትን ፍላጎት እንዴት ይመለከታሉ?" በሚል ከመከላከያ ሚዲያ ጋዜጠኞች ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል፤ "ኢትዮጵያ በጣም ትልቅ ሐገር ናት፣ በጣም ትልቅ የኢኮኖሚ ኃይልና ሕዝብም ያላት በመሆኑ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን አለባት ብለዋል። ከኢትዮጵያ ጋር የተካሄደው ወታደራዊ ትብብር ዋነኛ ዓላማም ፈረንሳይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ለማሻሻል አዲስ አበባ በመገኘቴ በጣም ኮርቻለሁ ብለዋል። ስለዚህ ትብብራችን በዋናነት የወታደራዊ ቁሳቁስ ድጋፍ ፣የሠላም ማስከበር ሥራዎች፣ የፈንጅ አወጋገድ ተግባራት ላይ፣ በሠው ኃይል ሥልጠና እና በሌሎችም ነው" ብለዋል። ጄነራል ፒየር ሺል ኢትዮጵያ የቀጠናውን ደኅንነት ለማስጠበቅ ዋነኛ ተዋናይ መሆኗን ገልፀው፣ የኢትዮጵያ ተሳትፎ እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና እንደ ፈረንሣይ ሠራዊት ተወካይ የኢትዮጵያን ሠራዊት እንደሚደግፉም አንስተዋል።   የኢትዮጵያን ሠራዊት ተሣትፎ በማድነቅ "ኢትዮጵያ በጣም ትልቅ ሐገር ናት፣ በጣም ጠንካራና ትልቅ ሠራዊትም አላት ከዚህ ሠራዊት ብዙ የምንማረው ነገር አለ ሲሉም አስረግጠው መናገራቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል። ከሰሞኑ በአዲስ አበባ የሚገኘው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዋናው መምሪያ የዓለም ኃያላንን ጨምሮ የተለያዩ ሐገራት የጦር መሪዎችን አስተናግዷል።
ትልልቅ የልማት አጀንዳዎችን ለማሳካት የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ የተግባቦት ሥራዎችን ማጠናከር ይገባል-ከፍተኛ አመራሮች
Nov 28, 2025 65
አዲስ አበባ፤ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ትልልቅ የልማት አጀንዳዎችን ለማሳካት የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ የተግባቦት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር አዘጋጅነት የፖለቲካ ትንተና፣ማህበራዊ ሚዲያና ሁኔታ ትንተና ላይ በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአሰልጣኞች ስልጠና መርሃ ግብር ተካሂዷል።   በሥልጠና መርሃ ግብሩ ላይ በፌደራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊዎችና የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትርና በብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል እንዳሉት፤ አመራሩ በሪፎርም ሥራዎች በመታገዝ ትልልቅ የልማት ግቦችን ለማሳካት እየተጋ ነው። እነዚህ የልማት ግቦች የሚሳኩት በሕዝቡና በመንግሥት መካከል መሰናሰል ሲፈጠር ነው ያሉት አቶ መላኩ፥ ህብረተሰቡን በልማት አጀንዳዎች ላይ በተሻለ መልኩ የሚያሳተፉ የተግባቦት ሥራዎችን በትኩረት ማከናወን ይገባል ብለዋል። አመራሩ እየተለዋወጠ ባለው የዓለም ሁኔታ ያሉ ዕድሎችን ለመጠቀም ወቅቱን የዋጀ እውቀት በመጨበጥ ህዝቡን በውጤታማነት የማሳተፍ ሥራን ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። ሥልጠናው በመረጃ ላይ በመመስረት ከሕዝቡ ጋር ይበልጥ ተናቦ ለመስራት ምቹ አውድ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።   የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙሳ አህመድ በበኩላቸው፥ በመደመር መንግሥት እይታ ፈጣንና ፈጠራ የታከለበት አገራዊ አድገት ለማረጋገጥ ግብ ተይዞ ወደ ሥራ ተገብቷል። ግቡን በውጤታማነት ለማጠናቀቅ በየጊዜው የፖለቲካ ትንተና ላይ የተመሰረቱ እርምጃዎች መውሰድ እንደሚገባ ጠቁመው፥ ለዚህም አመራሩ ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንዳለበት አመልክተዋል። የብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ መሀመድ እድሪስ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የኢኮኖሚ አመራሩ አካታች ኢኮኖሚ ግንባታ፣ ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና መሰል ጉዳዮች ላይ አጀንዳ ቀርጾ መሥራት ይጠበቅበታል።   የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የከተሞች ፎረምን ጨምሮ ሕዝቡን በማሳተፍ በውጤታማነት እየተተገበሩ ያሉ አጀንዳዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ መሰል ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። አመራሩ ፖሊሲዎችን ወደ አጀንዳነት መቀየር ላይ በሰፊው ሊሰራበት የሚገባው ጉዳይ ነው ብለዋል።   በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የብልፅግና ስትራቴጂ ጉዳይ ዋና ዳይሬክተር ተተካ በቀለ በበኩላቸው፤ የድህረ እውነት ፈተናዎች የሆኑትን ሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን መታገል ላይ አመራሩ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
አፍሪካ የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ ልማትና ዕድገቷን ለማረጋገጥ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች
Nov 28, 2025 59
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ ልማትና ዕድገቷን ለማረጋገጥ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ገለጹ። ፕሬዝደንቱ አፍሪካ በታሪኳ ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ ገልጸው፤ ተቋማትን ማጠናከር፣ ዲሞክራሲ፣ መረጋጋትና ዕድገት ወሳኝ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ 4ኛው የአፍሪካ ህገመንግስታዊ ፍርድ ቤቶች እና መሰል ተቋማት አለም አቀፍ ሲምፖዝየም "ህገ መንግስታዊነት እና ሀገረ መንግስት ግንባታ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።   የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ወቅት፤ አፍሪካ ለሕገ-መንግሥታዊነት እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የጀመረችውን ጥረት አጠናክራ ማስቀጠል ይኖርባታል ብለዋል፡፡ አፍሪካ ቁልፍ የሕዝብ አገልግሎቶችን መስጠት የሚችሉ የተረጋጋ ተቋማትን በመገንባት እና ተቋማዊ በማድረግ ረገድ በርካታ ስራዎች መሥራት እንደሚጠበቅባትም ገልጸዋል፡፡ የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥና የሰብአዊ መብቶችን ለማጠናከር የአስተዳደር ሁኔታን ከማሻሻል ባሻገር የአህጉሪቱን ልማት ማፋጠን መሠረታዊ መሆናቸውን አብራርተዋል።   የዚምባብዌ ጠቅላይ ዳኛ እና የአፍሪካ የሕገ-መንግሥት የዳኝነት አካላት ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሉክ ማላባ በበኩላቸው አህጉሪቱ ወደ አዲስ ምዕራፍ እየገባች መሆኗን ጠቁመው፤ አፍሪካውያን በራሳቸው መተማመንና የለውጥ አጀንዳቸውን መምራት እንደሚገባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። የአፍሪካ ህብረትን መሠረታዊ መርሆች ማስጠበቅ እና አፍሪካውያን የራሳቸውን የለውጥ አጀንዳዎች መምራት እንዲችሉ ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። አፍሪካ በወሳኝ ምእራፍ ላይ እንደምትገኝ የገለጹት ደግሞ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ጽሕፈት ቤት ዋና ኃላፊ አምባሳደር መሐመድ ኤል-አሚኒ ናቸው።   ተቋማትን ማጠናከር፣ዲሞክራሲ እንዲሁም ዕድገት ወሳኝ የሆነበት ወቅት መሆኑን ጠቁመዋል። ጠንካራና ነጻ የዳኝነት አካላት ሕጎች በፍትሐዊ መንገድ መተግበራቸውን፣ መብቶች መጠበቃቸውንና ሥልጣን በኃላፊነት መያዙን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸውን ጠቁመዋል።  

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን አለባት-የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል
Nov 28, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ። ከቀናት በፊት በሁለትዮሽ ወታደራዊ ጉዳዮች ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጄነራል መኮንኖች ጋር የመከሩት ጄነራል ፒየር ሺል የተለያዩ ተቋማትን ከጎበኙ በኋላ ከጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋርም ተወያይተዋል።   "ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ ለማግኘት ያላትን ፍላጎት እንዴት ይመለከታሉ?" በሚል ከመከላከያ ሚዲያ ጋዜጠኞች ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል፤ "ኢትዮጵያ በጣም ትልቅ ሐገር ናት፣ በጣም ትልቅ የኢኮኖሚ ኃይልና ሕዝብም ያላት በመሆኑ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን አለባት ብለዋል። ከኢትዮጵያ ጋር የተካሄደው ወታደራዊ ትብብር ዋነኛ ዓላማም ፈረንሳይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ለማሻሻል አዲስ አበባ በመገኘቴ በጣም ኮርቻለሁ ብለዋል። ስለዚህ ትብብራችን በዋናነት የወታደራዊ ቁሳቁስ ድጋፍ ፣የሠላም ማስከበር ሥራዎች፣ የፈንጅ አወጋገድ ተግባራት ላይ፣ በሠው ኃይል ሥልጠና እና በሌሎችም ነው" ብለዋል። ጄነራል ፒየር ሺል ኢትዮጵያ የቀጠናውን ደኅንነት ለማስጠበቅ ዋነኛ ተዋናይ መሆኗን ገልፀው፣ የኢትዮጵያ ተሳትፎ እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና እንደ ፈረንሣይ ሠራዊት ተወካይ የኢትዮጵያን ሠራዊት እንደሚደግፉም አንስተዋል።   የኢትዮጵያን ሠራዊት ተሣትፎ በማድነቅ "ኢትዮጵያ በጣም ትልቅ ሐገር ናት፣ በጣም ጠንካራና ትልቅ ሠራዊትም አላት ከዚህ ሠራዊት ብዙ የምንማረው ነገር አለ ሲሉም አስረግጠው መናገራቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል። ከሰሞኑ በአዲስ አበባ የሚገኘው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዋናው መምሪያ የዓለም ኃያላንን ጨምሮ የተለያዩ ሐገራት የጦር መሪዎችን አስተናግዷል።
ትልልቅ የልማት አጀንዳዎችን ለማሳካት የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ የተግባቦት ሥራዎችን ማጠናከር ይገባል-ከፍተኛ አመራሮች
Nov 28, 2025 65
አዲስ አበባ፤ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ትልልቅ የልማት አጀንዳዎችን ለማሳካት የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ የተግባቦት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር አዘጋጅነት የፖለቲካ ትንተና፣ማህበራዊ ሚዲያና ሁኔታ ትንተና ላይ በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአሰልጣኞች ስልጠና መርሃ ግብር ተካሂዷል።   በሥልጠና መርሃ ግብሩ ላይ በፌደራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊዎችና የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትርና በብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል እንዳሉት፤ አመራሩ በሪፎርም ሥራዎች በመታገዝ ትልልቅ የልማት ግቦችን ለማሳካት እየተጋ ነው። እነዚህ የልማት ግቦች የሚሳኩት በሕዝቡና በመንግሥት መካከል መሰናሰል ሲፈጠር ነው ያሉት አቶ መላኩ፥ ህብረተሰቡን በልማት አጀንዳዎች ላይ በተሻለ መልኩ የሚያሳተፉ የተግባቦት ሥራዎችን በትኩረት ማከናወን ይገባል ብለዋል። አመራሩ እየተለዋወጠ ባለው የዓለም ሁኔታ ያሉ ዕድሎችን ለመጠቀም ወቅቱን የዋጀ እውቀት በመጨበጥ ህዝቡን በውጤታማነት የማሳተፍ ሥራን ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። ሥልጠናው በመረጃ ላይ በመመስረት ከሕዝቡ ጋር ይበልጥ ተናቦ ለመስራት ምቹ አውድ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።   የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙሳ አህመድ በበኩላቸው፥ በመደመር መንግሥት እይታ ፈጣንና ፈጠራ የታከለበት አገራዊ አድገት ለማረጋገጥ ግብ ተይዞ ወደ ሥራ ተገብቷል። ግቡን በውጤታማነት ለማጠናቀቅ በየጊዜው የፖለቲካ ትንተና ላይ የተመሰረቱ እርምጃዎች መውሰድ እንደሚገባ ጠቁመው፥ ለዚህም አመራሩ ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንዳለበት አመልክተዋል። የብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ መሀመድ እድሪስ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የኢኮኖሚ አመራሩ አካታች ኢኮኖሚ ግንባታ፣ ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና መሰል ጉዳዮች ላይ አጀንዳ ቀርጾ መሥራት ይጠበቅበታል።   የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የከተሞች ፎረምን ጨምሮ ሕዝቡን በማሳተፍ በውጤታማነት እየተተገበሩ ያሉ አጀንዳዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ መሰል ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። አመራሩ ፖሊሲዎችን ወደ አጀንዳነት መቀየር ላይ በሰፊው ሊሰራበት የሚገባው ጉዳይ ነው ብለዋል።   በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የብልፅግና ስትራቴጂ ጉዳይ ዋና ዳይሬክተር ተተካ በቀለ በበኩላቸው፤ የድህረ እውነት ፈተናዎች የሆኑትን ሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን መታገል ላይ አመራሩ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ተማሪዎች ህብረ ብሔራዊ አብሮነትን እንዲላበሱ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 28, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ተማሪዎች ኢትዮጵያዊ ህብረ ብሔራዊነት አብሮነትን እንዲላበሱ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ርዕሳነ መምህራን ገለጹ። በየዓመቱ ህዳር 29 የሚከበረው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ዜጎች የአካባቢያቸውን አለባበስ፣ አመጋገብ፣ ቋንቋ፣ ባህልና እሴት የሚያስተዋውቁበት ታላቅ ኩነት ነው። ኢዜአ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በትውልዱ እንዲሰርጽ እና ህብረ ብሔራዊ አብሮነት እንዲጎለብት የትምህርት ተቋማት ሚናን በተመለከተ የትምህርት ባለሙያዎችን አነጋግሯል። የቂሊንጦ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢሳያስ ገብረሚካኤል፤ ኢትዮጵያ ብዝሃ ባህል ያላት በመሆኑ ይህንኑ ሀብት ለዓለም ለማስተዋወቅ ቀኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቅሰዋል። የትምህርት ዘርፉ ተዋናዮች ትውልዱ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ ውበት በአግባቡ በመገንዘብ ሀገሩን በተገቢው ልክ እንዲያውቅ የማስቻል አደራ አለብን ብለዋል። የአጋዚያን ቁጥር ሶስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርት ገነት ፊጣ በበኩላቸው፤ ቀኑ ትውፊቱን ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ በጋራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ለዚህም ሁላችንም የሌላውን ባህል የማክበር ልማዳችንን ማጠናከር አለብን ሲሉ ተናግረዋል። በተለይም ተማሪዎች የብሔር ብሔረሰቦችን ብዝሃ ባህል እና ማንነት በአግባቡ እንዲያውቁ ቀኑን መሰረት በማድረግ ግንዛቤአቸውን የማሳደግ ስራ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። የኮከበ ፅባህ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ደለለኝ አስማረ እንደሚሉት፤ ቀኑ ቀጣይነት ባለው መልኩ መከበሩ በህዝቦች መካከል ያለውን መልካም መስተጋብር የሚያጠናክር ነው። በዚሀም ተማሪዎች የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ያለውን ሀገራዊ ፋይዳ እንዲገነዘቡ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። ተማሪዎች የብሔሮችና ብሔረሰቦችን ባህል፣ ወግና እና እሴት በጭውውትና በክበባት አማካኝነት እንዲገነዘቡ እየሰሩ መሆኑን የድልበር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ መምህር ተመስገን ቶሊና አስታውቀዋል። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል "ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በሆሳዕና ከተማ ይከበራል።  
በተለያዩ አካባቢዎች እገታ እና ዘረፋ እየፈፀመ ባለው ፅንፈኛ ቡድን ላይ የተጠናከረ እርምጃ እየተወሰደ ነው
Nov 28, 2025 72
ባሕርዳር፤ ሕዳር 19/2018(ኢዜአ)፡- በተለያዩ አካባቢዎች እገታ እና ዘረፋ እየፈፀመ ባለው ፅንፈኛ ቡድን ላይ በሕዝቡና የጸጥታ ሃይሉ ትብብር የተጠናከረ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን የጃቢ ጠናን ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይችላል አድማሱ፤ በአካባቢው በፅንፈኛው ቡድን ላይ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በማፅናት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ፅንፈኛ ቡድኑ በጃቢ ጠናን ወረዳና አካባቢው በተለያዩ አጋጣሚዎች እየተሹለከለከ በነዋሪዎች ላይ እገታ፣ ዘረፋና ግድያ በመፈፀም ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር ለማድረግ መሞከሩን አንስተዋል። ከዚህም በመነሳት በሕዝቡ ጥቆማና ትብብር እንዲሁም በጸጥታ ኃይሉ የተጠና አካሄድ በፅንፈኛው ቡድኑ ላይ ጠንካራ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል። በዚህ የሕግ ማስከበር ስራም ከአርሶ አደሩ፣ ከባለሃብቶችና፣ ከእርሻ ልማት የተዘረፈ ከ649 ኩንታል በላይ እሕል ተከማችቶ መገኘቱን ጠቅሰዋል። በሕግ ማስከበር ስራ በተለይም የሕዝቡ ጥቆማ፣ ትብብርና እገዛ የላቀ መሆኑን አንስተው፤ በቀጣይም የተጠናከረ የሕግ ማስከበር ስራ ይከናወናል ሲሉ አረጋግጠዋል። በአማራ ክልል በዞን፣ በወረዳ እና ከተሞች የተለያዩ የማሕበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰሞኑን ተከታታይ ውይይቶች የተደረጉ ሲሆን፤በውይይቱም የፅንፈኛ ቡድኑ የጥፋት እንቅስቃሴ በስፋት የተነሳ መሆኑ ይታወቃል።
በስልጠናው የአካባቢ ጸጋዎችን ለይቶ ጥቅም ላይ በማዋል ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ግንዛቤ አግኝተናል
Nov 28, 2025 67
ሀዋሳ፤ህዳር 19/2018 (ኢዜአ)፡-የአካባቢ ጸጋዎችን ለይቶ ጥቅም ላይ በማዋል ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ግንዛቤ ማግኘታቸውን የሲዳማ ክልል ሰልጣኝ አመራሮች ተናገሩ። በክልሉ “በመደመር መንግስት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ ለመካከለኛና ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።   አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሥልጠናው ተሳታፊዎች በስልጠናው የአካባቢ ጸጋዎችን ለይቶ በማልማት ጥቅም ላይ ማዋልና ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ግንዛቤ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ከሰልጣኝ አመራሮች መካከል የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ሥራ አስፈፃሚ ኢያሱ ነጆ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የተቀናጀ የግብርና ምርት ኢንዱስትሪ ፓርኮች የግብርና ግብአቶችን በስፋት ይጠቀማሉ። በስልጠናው ግብርናውና ኢንዱስትሪው ተመጋግበው እንዴት ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና በዚህም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚቻልበት መንገድ ላይ ግንዛቤ መጨበጣቸውን ገልጸዋል። "በተለይ በአካባቢ ያሉና ያልታዩንን ጸጋዎች ጥቅም ላይ በማዋል ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባ አቅም የፈጠረልን ነው" ያሉት ኢያሱ (ዶ/ር) ፣ በቀጣይ ያገኙትን አቅም ተጠቅመው ለዘርፉ ለስኬታማነት ጠንክረው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መቅደስ ሁሪሶ በበኩላቸው እንዳሉት ከተማዋ የተለያዩ የቱሪስት መስህቦች ቢኖራትም ባላት ሀብት ልክ ፀጋዎቿን አልምቶ ጥቅም ላይ ማዋል አልተቻለም። ከስልጠናው በእጅ ያሉ ሀብቶችን ተጠቅሞ የሀዋሳን የቱሪስት መዳረሻነት ይበልጥ ማሳደግ እንደሚቻል ግንዛቤ ያገኙበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ የሀዋሳ ሐይቅ እና ታቦር ተራራን ጨምሮ የከተማዋ ነዋሪዎች ሠላማዊነትና እንግዳ ተቀባይነት ከተማዋን በጎብኚዎችና ባለሀብቶች ተመራጭ እንዳደረጋትም ጠቅሰዋል። በመሆኑም በቀጣይ ከኮሪደር ልማቱ ጋር ተያይዘው የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን በማጠናከር ገጽታዋን ይበልጥ ለማጉላትና ከዘርፉ የሚገኝ ጥቅምን ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል። ሥልጠናው አመራሩ በየሴክተሩ ያለውን አቅም ለይቶ ለውጤታማነት በቅንጅት መስራት የሚችልበትን አቅም የገነባበት ነው ያሉት ደግሞ የሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ደስታ ዳንቾ ናቸው፡፡ በተለይ የመንገድ መሠረተ ልማት ግብርናና ኢንዱስትሪው በተሳለጠ መልኩ እንዲመጋገቡ፣ የቱሪዝም ተደራሽነት እንዲሰፋና ሌሎች ልማቶች እንዲፋጠኑ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል ብለዋል። በመሆኑም ይህን የዘርፉን አስተዋጾ ለማጠናከር በስልጥና ያገኙትን አቅም ተጠቅመው ለውጤታማነት ተግተው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡ ለክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በተገኙበት ትናንት ማምሻውን እንደተጠናቀቀ መዘገቡ የሚታወስ ነው።    
የአማራና የኦሮሚያ ክልሎች ተጎራባች አካባቢ ነዋሪዎች የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን በጋራ አከበሩ
Nov 28, 2025 68
ደብረ ብርሃን፤ ሕዳር 19/ 2018(ኢዜአ)፡- የአማራና የኦሮሚያ ክልሎች አጎራባች አካባቢ ነዋሪዎች የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን የእህትማማችነትና የወንድማማችነት እሴትን በሚያጎለብት መልኩ በጋራ አከበሩ። በዓሉን በጋራ ያከበሩት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላና ጠራና በኦሮሚያ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ቅንቢቢት ወረዳዎች ተጎራባች አካባቢዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች ናቸው። በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የቅንቢቢት ወረዳ አፈ-ጉባዔ አቶ አስታጥቄ ገመቹ በበዓሉ ላይ ባደረጉት ንግግር የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በጋራ መከበር የሁለቱን አጎራባች ወረዳዎች ነዋሪዎች ትስስር ይበልጥ እንዲጠናከር ያደርጋል ብለዋል። በዓሉን በጋራ ስናከብርም ለዘመናት የዘለቀውን የእህትማማችነትና የወንድማማችነት እሴት በማጎልበት በአካባቢያችን ዘላቂ ሰላምን ለማፅናት ይበልጥ የሚያነሳሳ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የአንጎለላና ጠራና ቅንቢቢት ወረዳዎች አጎራባች ነዋሪዎች በባሕልና በማሕበራዊ ግንኙነት የተሳሰሩ በመሆኑ ትስስሩን ይበልጥ ለማጠናከር በጋራ መረባረብ እንደሚገባም አመልክተዋል። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የአንጎለላና ጠራ ወረዳ አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ገነት ይገዙ በበኩላቸው፤ በዓሉን በጋራ ስናከብር አንድነታችንን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላምና ልማት መጎልበት ለመሰራት በመነሳሳት ሊሆን ይገባል ብለዋል። የሁለቱ ተጎራባች ወረዳዎች ነዋሪዎች በባሕል፣ በጋብቻና በማሕበራዊ ግንኙነት ጠንካራ ትስስር እንዳላቸው ጠቁመው፤ ይህንን በማላቅ የተጀመሩ የልማትና የሰላም ስራዎች እንዲጠናከሩ በጋራ መስራታቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ከበዓሉ ተሳታፊዎች መካከል የአንጎለላና ጠራ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ኮኮቤ ማንበግሮት በሰጡት አስተያየት፤ በዓሉን በጋራ ማክበራቸው የጋራ ባሕልና እሴቶችን ለትውልድ ለማስተላለፍ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። የቅንቢቢት ወረዳ ነዋሪ አቶ ኩራባቸው ተክለስላሴ በበኩላቸው፤ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን በጋራ ማክበሩ አብሮነትን መሰረት ያደረገ ልማት ላይ በማተኮር እንድንተጋ ያግዛል ሲሉ ገልጸዋል። በሁለቱም ተጎራባች ወረዳዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ትስስራቸውን የበለጠ በማጎልበት ለጋራ እድገታቸው በቅንጅት እንደሚተጉ የበዓሉ ተሳታፊዎች አረጋግጠዋል።
ገዢ ትርክትን በመገንባት አንድነትንና ወንድማማችነትን ለማጎልበት የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ
Nov 28, 2025 72
ሚዛን አማን፣ ኅዳር 19/2018 (ኢዜአ)፡- ገዢ ትርክትን በመገንባት አንድነትንና ወንድማማችነትን ለማጎልበት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመላከተ። "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ክልላዊ የማጠቃለያ በዓል በሚዛን አማን ከተማ ተከብሯል።   በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንዳሉት ብዝሃነትን ማስተናገድና ፍትሃዊነትን ማረጋገጥ ለሀገር ግንባታ ትልቅ አቅም ነው። በዚህ ረገድ በክልሉ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ባህላቸውንና ቋንቋቸውን ለልማት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማበርከታቸውን አንስተዋል።   ይህን ተሞክሮ ለማስቀጠልም ነጠላ ትርክቶችን በማረም ገዢ ትርክትን በመገንባት አንድነትንና ወንድማማችነትን በማጎልበት ረገድ የተጀመሩ ተግባራትን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አመልክተዋል። የክልሉን ፀጋ ወደ ሀብት ቀይሮ ብልጽግናን ለማረጋገጥም ገዢ ትርክትን መገንባት መሰረታዊ ጉዳይ ነው ብለዋል።   የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በበኩላቸው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ባህልና ሌሎች እሴቶቻቸውን የሚያስተዋውቁበትን እድል ማስፋቱን ተናግረዋል። ሕገ መንግሥቱ ለብሔሮችና ብሔረሰቦች መብት መከበርና እኩልነት ያለው አበርክቶ ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር እንዳገዘም አመልክተዋል። አንድነትን በብዝኃነት ውስጥ በመገንባት ለልማት የሚውልበትን አቅም እናጠናክራለን ያሉት ደግሞ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ጌታቸው ኬኒ ናቸው።   ልዩነቶችን አክብሮ ለሀገር ብልጽግና መተባበር ላይ ሁሉም አቅሙን እንዲያዋጣም አሳስበዋል። ከበዓሉ ታዳሚዎች መካከል አቶ ሀብተማርያም ካዚንቴት እንዳሉት አሰባሳቢ ትርክትን ለመገንባት የበዓሉ መከበር የራሱ ድርሻ አለው።   በተለይም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በአንድነት ማክበራቸው ባህልና ቋንቋቸውን ለማሳደግና እርስ በርስ ለመተዋወቅ እንደሚያግዝም አክለዋል። በተለያየ ባህል፣ ቋንቋና ማንነት ውስጥ ያለውን የአብሮነት ትስስር ለትውልድ ለማስተላለፍ መሰል ኩነቶች ጠቃሚ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ ሌላው የበዓሉ ታዳሚ አቶ ፀጋዬ ኮርጅቴት ናቸው።  
የአፍሪካን ሰላም፣ አንድነትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሕገ መንግሥታዊ ስርዓትና ውጤታማ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ወሳኝ ነው
Nov 28, 2025 133
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ሰላም፣ አንድነትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሕገ መንግሥታዊ ስርዓትና ውጤታማ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለፁ። 4ኛው የአፍሪካ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤቶችና መሰል ተቋማት ዓለም አቀፍ ሲምፖዝየም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በመክፈቻ ንግግራቸው ሕገ መንግሥታዊ ስርዓት ህግ ከማውጣት ጋር የተያያዘ ብቻ ሳይሆን የህግ የበላይነትን ለማስከበር፣ ተጠያቂነትን ለማስፈንና መሰረታዊ መብቶች እንዲከበሩ የሚያስችል ነው ብለዋል። ሕገ መንግሥት የፖለቲካ ስልጣንን በኃላፊነት መወጣት የሚያስችል ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል።   አፍሪካ ሕገ መንግሥታዊ አስተዳደርን ለማስፈን የምታደርገው ጥረት የተለያዩ ተግዳሮቶች እየጋጠሙት እንደሚገኝም አንስተዋል። ስልጣንን በሕገ መንግሥታዊ ስርዓትና በህዝብ ድምፅ ከማግኘት ይልቅ በመፈንቅለ መንግሥትና በተቃውሞ የማግኘት ዝንባሌ በአህጉሪቱ ከሚገጥሙ ችግሮች መካከል መሆኑን ተናግረዋል። የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ተቋማዊ አቅም ማነስና ሕገ መንግሥታዊ ስርዓትን ያልተከተለ ስልጣን የማግኘት ፍላጎት ለአህጉሪቱ ሕገ መንግሥታዊ ጉዞ ፈተና የሆኑ ተግዳሮቶች መሆናቸውንም አንስተዋል። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የተለየ ልምድ ያላት ሀገር መሆኗን ጠቅሰው በንጉሳዊ ስርዓት የነበረው የፍትሐ-ነገሥት እንዲሁም እንደገዳ ስርዓት ያሉ ሀገር በቀል የሕግና አስተዳደር ስርዓቶች መኖራቸውን ተናግረዋል።   ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሕገ መንግሥት ያላት ሀገር መሆኗንም ነው ያነሱት። ሰላምና ብልፅግናዋ የተረጋገጠ የምንመኛትን አፍሪካ ለመፍጠር ፍትሃዊና በቅንነት የሚያገለግሉ የመንግሥት ተቋማትን መገንባት እንደሚገባ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። ለዚህም የሕገ መንግሥታዊ ስርዓት ግንባታ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ጠቁመው የስነዜጋ ትምህርትንና የዳኝነት ስርዓቱን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል። የአህጉሪቱን ሰላም፣ አንድነትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሕገ መንግሥታዊ ስርዓትና ውጤታማ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ገልፀዋል።
ፖለቲካ
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን አለባት-የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል
Nov 28, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ። ከቀናት በፊት በሁለትዮሽ ወታደራዊ ጉዳዮች ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጄነራል መኮንኖች ጋር የመከሩት ጄነራል ፒየር ሺል የተለያዩ ተቋማትን ከጎበኙ በኋላ ከጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋርም ተወያይተዋል።   "ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ ለማግኘት ያላትን ፍላጎት እንዴት ይመለከታሉ?" በሚል ከመከላከያ ሚዲያ ጋዜጠኞች ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል፤ "ኢትዮጵያ በጣም ትልቅ ሐገር ናት፣ በጣም ትልቅ የኢኮኖሚ ኃይልና ሕዝብም ያላት በመሆኑ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን አለባት ብለዋል። ከኢትዮጵያ ጋር የተካሄደው ወታደራዊ ትብብር ዋነኛ ዓላማም ፈረንሳይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ለማሻሻል አዲስ አበባ በመገኘቴ በጣም ኮርቻለሁ ብለዋል። ስለዚህ ትብብራችን በዋናነት የወታደራዊ ቁሳቁስ ድጋፍ ፣የሠላም ማስከበር ሥራዎች፣ የፈንጅ አወጋገድ ተግባራት ላይ፣ በሠው ኃይል ሥልጠና እና በሌሎችም ነው" ብለዋል። ጄነራል ፒየር ሺል ኢትዮጵያ የቀጠናውን ደኅንነት ለማስጠበቅ ዋነኛ ተዋናይ መሆኗን ገልፀው፣ የኢትዮጵያ ተሳትፎ እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና እንደ ፈረንሣይ ሠራዊት ተወካይ የኢትዮጵያን ሠራዊት እንደሚደግፉም አንስተዋል።   የኢትዮጵያን ሠራዊት ተሣትፎ በማድነቅ "ኢትዮጵያ በጣም ትልቅ ሐገር ናት፣ በጣም ጠንካራና ትልቅ ሠራዊትም አላት ከዚህ ሠራዊት ብዙ የምንማረው ነገር አለ ሲሉም አስረግጠው መናገራቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል። ከሰሞኑ በአዲስ አበባ የሚገኘው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዋናው መምሪያ የዓለም ኃያላንን ጨምሮ የተለያዩ ሐገራት የጦር መሪዎችን አስተናግዷል።
ትልልቅ የልማት አጀንዳዎችን ለማሳካት የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ የተግባቦት ሥራዎችን ማጠናከር ይገባል-ከፍተኛ አመራሮች
Nov 28, 2025 65
አዲስ አበባ፤ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ትልልቅ የልማት አጀንዳዎችን ለማሳካት የኅብረተሰቡን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ የተግባቦት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ። በብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር አዘጋጅነት የፖለቲካ ትንተና፣ማህበራዊ ሚዲያና ሁኔታ ትንተና ላይ በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የአሰልጣኞች ስልጠና መርሃ ግብር ተካሂዷል።   በሥልጠና መርሃ ግብሩ ላይ በፌደራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊዎችና የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትርና በብልፅግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አደረጃጀቶች የኢኮኖሚ ክላስተር ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል እንዳሉት፤ አመራሩ በሪፎርም ሥራዎች በመታገዝ ትልልቅ የልማት ግቦችን ለማሳካት እየተጋ ነው። እነዚህ የልማት ግቦች የሚሳኩት በሕዝቡና በመንግሥት መካከል መሰናሰል ሲፈጠር ነው ያሉት አቶ መላኩ፥ ህብረተሰቡን በልማት አጀንዳዎች ላይ በተሻለ መልኩ የሚያሳተፉ የተግባቦት ሥራዎችን በትኩረት ማከናወን ይገባል ብለዋል። አመራሩ እየተለዋወጠ ባለው የዓለም ሁኔታ ያሉ ዕድሎችን ለመጠቀም ወቅቱን የዋጀ እውቀት በመጨበጥ ህዝቡን በውጤታማነት የማሳተፍ ሥራን ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። ሥልጠናው በመረጃ ላይ በመመስረት ከሕዝቡ ጋር ይበልጥ ተናቦ ለመስራት ምቹ አውድ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።   የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙሳ አህመድ በበኩላቸው፥ በመደመር መንግሥት እይታ ፈጣንና ፈጠራ የታከለበት አገራዊ አድገት ለማረጋገጥ ግብ ተይዞ ወደ ሥራ ተገብቷል። ግቡን በውጤታማነት ለማጠናቀቅ በየጊዜው የፖለቲካ ትንተና ላይ የተመሰረቱ እርምጃዎች መውሰድ እንደሚገባ ጠቁመው፥ ለዚህም አመራሩ ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንዳለበት አመልክተዋል። የብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ መሀመድ እድሪስ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የኢኮኖሚ አመራሩ አካታች ኢኮኖሚ ግንባታ፣ ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና መሰል ጉዳዮች ላይ አጀንዳ ቀርጾ መሥራት ይጠበቅበታል።   የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የከተሞች ፎረምን ጨምሮ ሕዝቡን በማሳተፍ በውጤታማነት እየተተገበሩ ያሉ አጀንዳዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ መሰል ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። አመራሩ ፖሊሲዎችን ወደ አጀንዳነት መቀየር ላይ በሰፊው ሊሰራበት የሚገባው ጉዳይ ነው ብለዋል።   በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የብልፅግና ስትራቴጂ ጉዳይ ዋና ዳይሬክተር ተተካ በቀለ በበኩላቸው፤ የድህረ እውነት ፈተናዎች የሆኑትን ሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን መታገል ላይ አመራሩ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ተማሪዎች ህብረ ብሔራዊ አብሮነትን እንዲላበሱ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 28, 2025 51
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ተማሪዎች ኢትዮጵያዊ ህብረ ብሔራዊነት አብሮነትን እንዲላበሱ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ርዕሳነ መምህራን ገለጹ። በየዓመቱ ህዳር 29 የሚከበረው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ዜጎች የአካባቢያቸውን አለባበስ፣ አመጋገብ፣ ቋንቋ፣ ባህልና እሴት የሚያስተዋውቁበት ታላቅ ኩነት ነው። ኢዜአ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በትውልዱ እንዲሰርጽ እና ህብረ ብሔራዊ አብሮነት እንዲጎለብት የትምህርት ተቋማት ሚናን በተመለከተ የትምህርት ባለሙያዎችን አነጋግሯል። የቂሊንጦ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢሳያስ ገብረሚካኤል፤ ኢትዮጵያ ብዝሃ ባህል ያላት በመሆኑ ይህንኑ ሀብት ለዓለም ለማስተዋወቅ ቀኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቅሰዋል። የትምህርት ዘርፉ ተዋናዮች ትውልዱ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ ውበት በአግባቡ በመገንዘብ ሀገሩን በተገቢው ልክ እንዲያውቅ የማስቻል አደራ አለብን ብለዋል። የአጋዚያን ቁጥር ሶስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርት ገነት ፊጣ በበኩላቸው፤ ቀኑ ትውፊቱን ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ በጋራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ለዚህም ሁላችንም የሌላውን ባህል የማክበር ልማዳችንን ማጠናከር አለብን ሲሉ ተናግረዋል። በተለይም ተማሪዎች የብሔር ብሔረሰቦችን ብዝሃ ባህል እና ማንነት በአግባቡ እንዲያውቁ ቀኑን መሰረት በማድረግ ግንዛቤአቸውን የማሳደግ ስራ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። የኮከበ ፅባህ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ደለለኝ አስማረ እንደሚሉት፤ ቀኑ ቀጣይነት ባለው መልኩ መከበሩ በህዝቦች መካከል ያለውን መልካም መስተጋብር የሚያጠናክር ነው። በዚሀም ተማሪዎች የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ያለውን ሀገራዊ ፋይዳ እንዲገነዘቡ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። ተማሪዎች የብሔሮችና ብሔረሰቦችን ባህል፣ ወግና እና እሴት በጭውውትና በክበባት አማካኝነት እንዲገነዘቡ እየሰሩ መሆኑን የድልበር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ መምህር ተመስገን ቶሊና አስታውቀዋል። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል "ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በሆሳዕና ከተማ ይከበራል።  
በተለያዩ አካባቢዎች እገታ እና ዘረፋ እየፈፀመ ባለው ፅንፈኛ ቡድን ላይ የተጠናከረ እርምጃ እየተወሰደ ነው
Nov 28, 2025 72
ባሕርዳር፤ ሕዳር 19/2018(ኢዜአ)፡- በተለያዩ አካባቢዎች እገታ እና ዘረፋ እየፈፀመ ባለው ፅንፈኛ ቡድን ላይ በሕዝቡና የጸጥታ ሃይሉ ትብብር የተጠናከረ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን የጃቢ ጠናን ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይችላል አድማሱ፤ በአካባቢው በፅንፈኛው ቡድን ላይ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በማፅናት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ፅንፈኛ ቡድኑ በጃቢ ጠናን ወረዳና አካባቢው በተለያዩ አጋጣሚዎች እየተሹለከለከ በነዋሪዎች ላይ እገታ፣ ዘረፋና ግድያ በመፈፀም ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር ለማድረግ መሞከሩን አንስተዋል። ከዚህም በመነሳት በሕዝቡ ጥቆማና ትብብር እንዲሁም በጸጥታ ኃይሉ የተጠና አካሄድ በፅንፈኛው ቡድኑ ላይ ጠንካራ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል። በዚህ የሕግ ማስከበር ስራም ከአርሶ አደሩ፣ ከባለሃብቶችና፣ ከእርሻ ልማት የተዘረፈ ከ649 ኩንታል በላይ እሕል ተከማችቶ መገኘቱን ጠቅሰዋል። በሕግ ማስከበር ስራ በተለይም የሕዝቡ ጥቆማ፣ ትብብርና እገዛ የላቀ መሆኑን አንስተው፤ በቀጣይም የተጠናከረ የሕግ ማስከበር ስራ ይከናወናል ሲሉ አረጋግጠዋል። በአማራ ክልል በዞን፣ በወረዳ እና ከተሞች የተለያዩ የማሕበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰሞኑን ተከታታይ ውይይቶች የተደረጉ ሲሆን፤በውይይቱም የፅንፈኛ ቡድኑ የጥፋት እንቅስቃሴ በስፋት የተነሳ መሆኑ ይታወቃል።
በስልጠናው የአካባቢ ጸጋዎችን ለይቶ ጥቅም ላይ በማዋል ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ግንዛቤ አግኝተናል
Nov 28, 2025 67
ሀዋሳ፤ህዳር 19/2018 (ኢዜአ)፡-የአካባቢ ጸጋዎችን ለይቶ ጥቅም ላይ በማዋል ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ግንዛቤ ማግኘታቸውን የሲዳማ ክልል ሰልጣኝ አመራሮች ተናገሩ። በክልሉ “በመደመር መንግስት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ ለመካከለኛና ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።   አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሥልጠናው ተሳታፊዎች በስልጠናው የአካባቢ ጸጋዎችን ለይቶ በማልማት ጥቅም ላይ ማዋልና ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ግንዛቤ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ከሰልጣኝ አመራሮች መካከል የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ሥራ አስፈፃሚ ኢያሱ ነጆ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የተቀናጀ የግብርና ምርት ኢንዱስትሪ ፓርኮች የግብርና ግብአቶችን በስፋት ይጠቀማሉ። በስልጠናው ግብርናውና ኢንዱስትሪው ተመጋግበው እንዴት ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና በዚህም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚቻልበት መንገድ ላይ ግንዛቤ መጨበጣቸውን ገልጸዋል። "በተለይ በአካባቢ ያሉና ያልታዩንን ጸጋዎች ጥቅም ላይ በማዋል ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባ አቅም የፈጠረልን ነው" ያሉት ኢያሱ (ዶ/ር) ፣ በቀጣይ ያገኙትን አቅም ተጠቅመው ለዘርፉ ለስኬታማነት ጠንክረው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መቅደስ ሁሪሶ በበኩላቸው እንዳሉት ከተማዋ የተለያዩ የቱሪስት መስህቦች ቢኖራትም ባላት ሀብት ልክ ፀጋዎቿን አልምቶ ጥቅም ላይ ማዋል አልተቻለም። ከስልጠናው በእጅ ያሉ ሀብቶችን ተጠቅሞ የሀዋሳን የቱሪስት መዳረሻነት ይበልጥ ማሳደግ እንደሚቻል ግንዛቤ ያገኙበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ የሀዋሳ ሐይቅ እና ታቦር ተራራን ጨምሮ የከተማዋ ነዋሪዎች ሠላማዊነትና እንግዳ ተቀባይነት ከተማዋን በጎብኚዎችና ባለሀብቶች ተመራጭ እንዳደረጋትም ጠቅሰዋል። በመሆኑም በቀጣይ ከኮሪደር ልማቱ ጋር ተያይዘው የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን በማጠናከር ገጽታዋን ይበልጥ ለማጉላትና ከዘርፉ የሚገኝ ጥቅምን ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል። ሥልጠናው አመራሩ በየሴክተሩ ያለውን አቅም ለይቶ ለውጤታማነት በቅንጅት መስራት የሚችልበትን አቅም የገነባበት ነው ያሉት ደግሞ የሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ደስታ ዳንቾ ናቸው፡፡ በተለይ የመንገድ መሠረተ ልማት ግብርናና ኢንዱስትሪው በተሳለጠ መልኩ እንዲመጋገቡ፣ የቱሪዝም ተደራሽነት እንዲሰፋና ሌሎች ልማቶች እንዲፋጠኑ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል ብለዋል። በመሆኑም ይህን የዘርፉን አስተዋጾ ለማጠናከር በስልጥና ያገኙትን አቅም ተጠቅመው ለውጤታማነት ተግተው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡ ለክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በተገኙበት ትናንት ማምሻውን እንደተጠናቀቀ መዘገቡ የሚታወስ ነው።    
የአማራና የኦሮሚያ ክልሎች ተጎራባች አካባቢ ነዋሪዎች የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን በጋራ አከበሩ
Nov 28, 2025 68
ደብረ ብርሃን፤ ሕዳር 19/ 2018(ኢዜአ)፡- የአማራና የኦሮሚያ ክልሎች አጎራባች አካባቢ ነዋሪዎች የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን የእህትማማችነትና የወንድማማችነት እሴትን በሚያጎለብት መልኩ በጋራ አከበሩ። በዓሉን በጋራ ያከበሩት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላና ጠራና በኦሮሚያ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ቅንቢቢት ወረዳዎች ተጎራባች አካባቢዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች ናቸው። በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የቅንቢቢት ወረዳ አፈ-ጉባዔ አቶ አስታጥቄ ገመቹ በበዓሉ ላይ ባደረጉት ንግግር የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በጋራ መከበር የሁለቱን አጎራባች ወረዳዎች ነዋሪዎች ትስስር ይበልጥ እንዲጠናከር ያደርጋል ብለዋል። በዓሉን በጋራ ስናከብርም ለዘመናት የዘለቀውን የእህትማማችነትና የወንድማማችነት እሴት በማጎልበት በአካባቢያችን ዘላቂ ሰላምን ለማፅናት ይበልጥ የሚያነሳሳ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የአንጎለላና ጠራና ቅንቢቢት ወረዳዎች አጎራባች ነዋሪዎች በባሕልና በማሕበራዊ ግንኙነት የተሳሰሩ በመሆኑ ትስስሩን ይበልጥ ለማጠናከር በጋራ መረባረብ እንደሚገባም አመልክተዋል። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የአንጎለላና ጠራ ወረዳ አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ገነት ይገዙ በበኩላቸው፤ በዓሉን በጋራ ስናከብር አንድነታችንን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላምና ልማት መጎልበት ለመሰራት በመነሳሳት ሊሆን ይገባል ብለዋል። የሁለቱ ተጎራባች ወረዳዎች ነዋሪዎች በባሕል፣ በጋብቻና በማሕበራዊ ግንኙነት ጠንካራ ትስስር እንዳላቸው ጠቁመው፤ ይህንን በማላቅ የተጀመሩ የልማትና የሰላም ስራዎች እንዲጠናከሩ በጋራ መስራታቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ከበዓሉ ተሳታፊዎች መካከል የአንጎለላና ጠራ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ኮኮቤ ማንበግሮት በሰጡት አስተያየት፤ በዓሉን በጋራ ማክበራቸው የጋራ ባሕልና እሴቶችን ለትውልድ ለማስተላለፍ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። የቅንቢቢት ወረዳ ነዋሪ አቶ ኩራባቸው ተክለስላሴ በበኩላቸው፤ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን በጋራ ማክበሩ አብሮነትን መሰረት ያደረገ ልማት ላይ በማተኮር እንድንተጋ ያግዛል ሲሉ ገልጸዋል። በሁለቱም ተጎራባች ወረዳዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ትስስራቸውን የበለጠ በማጎልበት ለጋራ እድገታቸው በቅንጅት እንደሚተጉ የበዓሉ ተሳታፊዎች አረጋግጠዋል።
ገዢ ትርክትን በመገንባት አንድነትንና ወንድማማችነትን ለማጎልበት የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ
Nov 28, 2025 72
ሚዛን አማን፣ ኅዳር 19/2018 (ኢዜአ)፡- ገዢ ትርክትን በመገንባት አንድነትንና ወንድማማችነትን ለማጎልበት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመላከተ። "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ክልላዊ የማጠቃለያ በዓል በሚዛን አማን ከተማ ተከብሯል።   በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንዳሉት ብዝሃነትን ማስተናገድና ፍትሃዊነትን ማረጋገጥ ለሀገር ግንባታ ትልቅ አቅም ነው። በዚህ ረገድ በክልሉ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ባህላቸውንና ቋንቋቸውን ለልማት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማበርከታቸውን አንስተዋል።   ይህን ተሞክሮ ለማስቀጠልም ነጠላ ትርክቶችን በማረም ገዢ ትርክትን በመገንባት አንድነትንና ወንድማማችነትን በማጎልበት ረገድ የተጀመሩ ተግባራትን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አመልክተዋል። የክልሉን ፀጋ ወደ ሀብት ቀይሮ ብልጽግናን ለማረጋገጥም ገዢ ትርክትን መገንባት መሰረታዊ ጉዳይ ነው ብለዋል።   የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በበኩላቸው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ባህልና ሌሎች እሴቶቻቸውን የሚያስተዋውቁበትን እድል ማስፋቱን ተናግረዋል። ሕገ መንግሥቱ ለብሔሮችና ብሔረሰቦች መብት መከበርና እኩልነት ያለው አበርክቶ ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር እንዳገዘም አመልክተዋል። አንድነትን በብዝኃነት ውስጥ በመገንባት ለልማት የሚውልበትን አቅም እናጠናክራለን ያሉት ደግሞ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ጌታቸው ኬኒ ናቸው።   ልዩነቶችን አክብሮ ለሀገር ብልጽግና መተባበር ላይ ሁሉም አቅሙን እንዲያዋጣም አሳስበዋል። ከበዓሉ ታዳሚዎች መካከል አቶ ሀብተማርያም ካዚንቴት እንዳሉት አሰባሳቢ ትርክትን ለመገንባት የበዓሉ መከበር የራሱ ድርሻ አለው።   በተለይም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በአንድነት ማክበራቸው ባህልና ቋንቋቸውን ለማሳደግና እርስ በርስ ለመተዋወቅ እንደሚያግዝም አክለዋል። በተለያየ ባህል፣ ቋንቋና ማንነት ውስጥ ያለውን የአብሮነት ትስስር ለትውልድ ለማስተላለፍ መሰል ኩነቶች ጠቃሚ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ ሌላው የበዓሉ ታዳሚ አቶ ፀጋዬ ኮርጅቴት ናቸው።  
የአፍሪካን ሰላም፣ አንድነትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሕገ መንግሥታዊ ስርዓትና ውጤታማ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ወሳኝ ነው
Nov 28, 2025 133
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ሰላም፣ አንድነትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሕገ መንግሥታዊ ስርዓትና ውጤታማ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለፁ። 4ኛው የአፍሪካ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤቶችና መሰል ተቋማት ዓለም አቀፍ ሲምፖዝየም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በመክፈቻ ንግግራቸው ሕገ መንግሥታዊ ስርዓት ህግ ከማውጣት ጋር የተያያዘ ብቻ ሳይሆን የህግ የበላይነትን ለማስከበር፣ ተጠያቂነትን ለማስፈንና መሰረታዊ መብቶች እንዲከበሩ የሚያስችል ነው ብለዋል። ሕገ መንግሥት የፖለቲካ ስልጣንን በኃላፊነት መወጣት የሚያስችል ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል።   አፍሪካ ሕገ መንግሥታዊ አስተዳደርን ለማስፈን የምታደርገው ጥረት የተለያዩ ተግዳሮቶች እየጋጠሙት እንደሚገኝም አንስተዋል። ስልጣንን በሕገ መንግሥታዊ ስርዓትና በህዝብ ድምፅ ከማግኘት ይልቅ በመፈንቅለ መንግሥትና በተቃውሞ የማግኘት ዝንባሌ በአህጉሪቱ ከሚገጥሙ ችግሮች መካከል መሆኑን ተናግረዋል። የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ተቋማዊ አቅም ማነስና ሕገ መንግሥታዊ ስርዓትን ያልተከተለ ስልጣን የማግኘት ፍላጎት ለአህጉሪቱ ሕገ መንግሥታዊ ጉዞ ፈተና የሆኑ ተግዳሮቶች መሆናቸውንም አንስተዋል። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የተለየ ልምድ ያላት ሀገር መሆኗን ጠቅሰው በንጉሳዊ ስርዓት የነበረው የፍትሐ-ነገሥት እንዲሁም እንደገዳ ስርዓት ያሉ ሀገር በቀል የሕግና አስተዳደር ስርዓቶች መኖራቸውን ተናግረዋል።   ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሕገ መንግሥት ያላት ሀገር መሆኗንም ነው ያነሱት። ሰላምና ብልፅግናዋ የተረጋገጠ የምንመኛትን አፍሪካ ለመፍጠር ፍትሃዊና በቅንነት የሚያገለግሉ የመንግሥት ተቋማትን መገንባት እንደሚገባ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። ለዚህም የሕገ መንግሥታዊ ስርዓት ግንባታ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ጠቁመው የስነዜጋ ትምህርትንና የዳኝነት ስርዓቱን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል። የአህጉሪቱን ሰላም፣ አንድነትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሕገ መንግሥታዊ ስርዓትና ውጤታማ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ገልፀዋል።
ማህበራዊ
የበለፀገችና ህብረብሄራዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና መወጣት አለባቸው - ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር)
Nov 28, 2025 40
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ አንድነቷ የጸና የበለፀገችና ህብረብሄራዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ወጣቶች ውይይት ለሰላም ማህበር ጋር በመተባበር ወጣቶች ለሰላም ግንባታና ለማህበራዊ ትስስር መጠናከር በሚኖራቸው ሚና ላይ ያተኮረ "አዲስ ፎረም 2025" እየተካሄደ ይገኛል።   የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ወጣቶች ለሰላም፣ አንድነት፣ አብሮነት፣ ለሀገር ብልፅግና ወሳኝ ሚና አላቸው፡፡ መንግሥት አስቻይ ሁኔታዎችን በመፍጠር ወጣቶች ለሀገር ልማት የበኩላቸውን እንዲወጡ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። አንድነቷ የፀና፣ የበለፀገችና ህብረብሄራዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት ወጣቶች ያላቸውን አቅም በመጠቀም ሚናቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል፡፡ "የኢትዮጵያ ወጣቶች ለሰላምና ደህንነት ሀገራዊ የድርጊት መርሃግብር" መጠናቀቁን የገለጹት ሚኒስትሯ፤ ለገቢራዊነቱ የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶች እና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር ቀጀላ መርዳሳ በበኩላቸው፤ ወጣቶች ግንባር ቀደም የሰላም ዘብ የመሆን ሀገራዊ ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። ለዘላቂ ልማትና ኢኮኖሚያዊ እድገት የወጣቶች ሚና ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ ወጣቶች ልማት ላይ በስፋት እንዲሳተፉ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ለአመራርነት ለማብቃት በክህሎት ልማት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡   የኢትዮጵያ ወጣቶች ውይይት ለሰላም ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወጣት ኢንጂነር ጫላ አሰፋ፤ ሰላም እያንዳንዳችን የምንገነባው የጋራ ህንፃ መሆኑን ገልጿል። ሰላም የሁሉ ነገር መነሻና መሰረት፤ ለልማትና አንድነት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ ማህበሩ ወጣቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ መሀንዲስ፣ የለውጥ መሪ እንዲሆኑም ተናግሯል። የፎረሙ ተሳታፊ ወጣቶች በበኩላቸው ወጣቶች በሀገር ግንባታና ሰላም የላቀ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸው የሚናቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡
ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ዘላቂ ልማትን በማረጋገጥ ሂደት ወሳኝ ሚና ሊጫወቱ ይገባል -ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
Nov 28, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሀገራዊና አህጉራዊ ዘላቂ ልማትን በማረጋገጥ ሂደት ወሳኝ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ75ኛ ዓመት አልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል አካል የሆነ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አጋሮች መርሃ ግብር ተካሂዷል።   በመርኃ ግብሩ የትምህርት ሚኒስትርና የዩኒቨርሲቲው ቻንስለር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር)፣ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት አብረው የተጓዙ አጋሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በዚህም "ለዘላቂ ልማት እና ለአፍሪካ መጻኢ ዕጣ ፈንታ የከፍተኛ ትምህርት ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ለሀገራት ሁለንተናዊ እድገት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና ወሳኝ ነው። የተማረ የሰው ኃይልን በማፍራት እንዲሁም በጥናትና ምርምር ስራዎች ዘላቂ ልማትን የማረጋገጥ ሂደት ላይ አሻራቸውን ማሳረፍ ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።   የደቡብ ደቡብ ትብብር ምክትል ዋና ፀሐፊ ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም በበኩላቸው፤ ዘላቂ ልማት የሚለካው በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ብቻ ሳይሆን በእውቀትና በእሴት መጎልበት እንዲሁም በማህበረሰብ ለውጥ ጭምር መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዘላቂ ልማት መረጋገጥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያላቸው ሚና ቁልፍ መሆኑንም አስረድተዋል። በመድረኩ የፓናል ውይይት ተሳታፊ የሆኑት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዘላቂ ልማት ላይ ስርዓተ ትምህርት ቀርፀው መስራት እንዳለባቸው አመላክተዋል።   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ የድህረ ምረቃ ጥናትና ምርምር ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጽጌ ገብረማርያም፥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማህበረሰብ ተኮር ምርምር እና ፈጠራ ላይ የማተኮር ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት በጥናት ላይ የተመሠረተ የፖሊሲ አወጣጥ ላይ የሚያበረክቱት አስተዋፅዖ ወሳኝ እንደሆነ የተናገሩት ደግሞ የባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ ናቸው። በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች የሀገራዊ የፖሊሲ ውሳኔዎችን ለማዘጋጀት የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶችን ማፍለቅ እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የፍትህ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ሀገራዊ ሪፎርም አድርጋለች
Nov 28, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የፍትህ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ሀገራዊ ሪፎርም ማድረጓን የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) ገለጹ። የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ ከፍትሕ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ፈዴራል ጠበቆች ማህበር ጋር በመተባበር 30ኛ ዓመት የምሥረታና ዓመታዊ ጉባኤውን በአፍሪካ ሕብረት ማካሄድ ጀምሯል፡፡ የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በለውጡ ዓመታት ከሀገር አልፎ ቀጣናውን የሚያስተሳስሩ የዲሞክራሲ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ጥረት እያደረገች ነው።   በዚህም ባለፉት ዓመታት ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የፍትህ ተቋማትን መፍጠር የሚያስችል ሀገራዊ ሪፎርም ማድረጓን ተናግረዋል። በፍትህ ዘርፉ የተደረገው ሪፎርም የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ህጋዊና ገለልተኛ ተቋም ሆኖ እንዲፈጠር አስችሏል ብለዋል። የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ከአምስቱ የፍትህ ዘርፍ መሰረቶች አንዱ እንዲሆን መደረጉን ገልጸዋል። ይሄውም ኢትዮጵያ በሀገራዊ ሪፎርሙ የፍትህ ተቋማትን ለማጠናከር የወሰደችውን ወሳኝ እርምጃ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበርና የሌሎች የቀጣናው ሀገራት የፍትሕ ተቋማት ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው አንስተዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ጽህፈት ቤት ዋና ኃላፊ አምባሳደር ሞሐመድ ኤል አሚን ሱፍ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063ን ግብ ለማሳካት ያግዛል ብለዋል።   በአፍሪካ ሀገራት ወደ መድብለ ፓርቲ ስርዓት በሚያደርጉት ሽግግር የፖለቲካ መረጋጋትን ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት መልካም አስተዳደር ዲሞክራሲና ፍትሕን ለማስፈን የሚሰሩበት ጊዜ አሁን ነው ያሉት ሀላፊው፤ ሕብረቱ የተለያዩ የዲሞክራሲ ተቋማትን በማቋቋም ለፍትህ ስርዓት መስፈን አባል ሀገራትን እየደገፈ ነው ብለዋል። የአፍሪካ የዲሞክራሲ አስተዳደርና የምርጫ ቻርተር፣ የአፍሪካ ሰላምና ደህንነት አርክቴክቸር ግጭትን በመከላከል ሰላምን ማስፈን የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረት የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የያዛቸውን አጀንዳዎች ከግብ ለማድረስ የፍትሕ ተቋማትና የህግ ባለሙያዎች ለመልካም አስተዳደር መስፈንና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል፡፡ የሕብረቱ አባል ሀገራት የጋራ እሴቶቻቸውን በማጎልበት በትብብር መስራት እንዳለባቸው ገልጸው፤ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ወጣት የህግ ባለሙያዎችን በማሰልጠን ለህግ የበላይነትና መልካም አስተዳደር መስፈን ሚናውን መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡   የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ ፕሬዝዳንት ረመዳን አቡበከር፤ ተቋሙ በቀጣናው ፍትሕን በማረጋገጥ የህግ የበላይነት የማስፈን ኃላፊነት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ የሕግ የበላይነትና ዲሞክራሲ በራሱ የሚቀጥል ሳይሆን በየጊዜው ልምምድን የሚጠይቅ መሆኑን በማንሳት፤ የዲሞክራሲ ተቋማትን መገንባት ካልተቻለ አለመረጋጋት ይፈጠራል ብለዋል፡፡ የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ በሽዎች የሚቆጠሩ ወጣት የህግ ባለሙያዎችን በማሰልጠን ለአፍሪካ ሕብረት መልካም አስተዳደር፣ ሰብዓዊ መብትና ዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ግብ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቀጣናው በተከፋፈለ መንገድ ንግድና ኢንቨስትመንትን ማሳደግ እንደማይቻል ገልጸው፤ የምሥራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ በሀገራት መካከል የህግ ስርዓት ትብብር እንዲፈጠር ሚናውን ይወጣል ብለዋል፡፡ ከዚህ አንፃር የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር ኢትዮጵያ በፍትህ ተቋማትን ለማጠናከር የጀመረችውን እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ጌታቸው የምስራቅ አፍሪካ የህግ በማህበረሰብ የቀጣናው ስትራቴጂካዊ አጋር ሆኖ እንደሚቀጠል ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ዜጎችን የፍትሕ እጦት ለመፍታት፣ ለህግ የበላይነት መረጋገጥ ሚናውን ይወጣል ብለዋል፡፡ ከምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ጋር በትብብር በመስራት የቀጣናውን ንግድና ኢንቨስትመንት ለማሳለጥ አበክሮ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ለፍትህ ዘርፉ ዕድገት ገንቢ ሚና እንዳለው በማንሳት፤ ተቋሙን ለማጠናከር አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል ብለዋል፡፡      
አፍሪካ የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ ልማትና ዕድገቷን ለማረጋገጥ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች
Nov 28, 2025 59
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ ልማትና ዕድገቷን ለማረጋገጥ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ገለጹ። ፕሬዝደንቱ አፍሪካ በታሪኳ ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ ገልጸው፤ ተቋማትን ማጠናከር፣ ዲሞክራሲ፣ መረጋጋትና ዕድገት ወሳኝ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ 4ኛው የአፍሪካ ህገመንግስታዊ ፍርድ ቤቶች እና መሰል ተቋማት አለም አቀፍ ሲምፖዝየም "ህገ መንግስታዊነት እና ሀገረ መንግስት ግንባታ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።   የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ወቅት፤ አፍሪካ ለሕገ-መንግሥታዊነት እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የጀመረችውን ጥረት አጠናክራ ማስቀጠል ይኖርባታል ብለዋል፡፡ አፍሪካ ቁልፍ የሕዝብ አገልግሎቶችን መስጠት የሚችሉ የተረጋጋ ተቋማትን በመገንባት እና ተቋማዊ በማድረግ ረገድ በርካታ ስራዎች መሥራት እንደሚጠበቅባትም ገልጸዋል፡፡ የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥና የሰብአዊ መብቶችን ለማጠናከር የአስተዳደር ሁኔታን ከማሻሻል ባሻገር የአህጉሪቱን ልማት ማፋጠን መሠረታዊ መሆናቸውን አብራርተዋል።   የዚምባብዌ ጠቅላይ ዳኛ እና የአፍሪካ የሕገ-መንግሥት የዳኝነት አካላት ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሉክ ማላባ በበኩላቸው አህጉሪቱ ወደ አዲስ ምዕራፍ እየገባች መሆኗን ጠቁመው፤ አፍሪካውያን በራሳቸው መተማመንና የለውጥ አጀንዳቸውን መምራት እንደሚገባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። የአፍሪካ ህብረትን መሠረታዊ መርሆች ማስጠበቅ እና አፍሪካውያን የራሳቸውን የለውጥ አጀንዳዎች መምራት እንዲችሉ ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። አፍሪካ በወሳኝ ምእራፍ ላይ እንደምትገኝ የገለጹት ደግሞ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ጽሕፈት ቤት ዋና ኃላፊ አምባሳደር መሐመድ ኤል-አሚኒ ናቸው።   ተቋማትን ማጠናከር፣ዲሞክራሲ እንዲሁም ዕድገት ወሳኝ የሆነበት ወቅት መሆኑን ጠቁመዋል። ጠንካራና ነጻ የዳኝነት አካላት ሕጎች በፍትሐዊ መንገድ መተግበራቸውን፣ መብቶች መጠበቃቸውንና ሥልጣን በኃላፊነት መያዙን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸውን ጠቁመዋል።  
ኢኮኖሚ
የሀረር የኮሪደር ልማት የጀጎል ዓለም አቀፍ ቅርስን ከመጠበቅም ባለፈ ለጎብኚዎች ምቹና ማራኪ እንዲሆን አስችሎታል
Nov 28, 2025 59
ሐረር፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ):- የሀረር የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎች የጀጎል ዓለም አቀፍ ቅርስን ከመጠበቅም ባለፈ ለጎብኚዎች ምቹና ማራኪ እንዲሆን አስችሎታል ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ተናገሩ። በቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፤ የተመራው የአምባሳደሮችና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዑካን ቡድን በሀረሪ ክልል የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን ጎብኝቷል። የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ፤ የመርሃ ግብሩ ዓላማ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) እና የቱሪዝም ሚኒስቴር በመተባበር የቱሪዝም መዳረሻዎችንና ሃብቶችን የመጎብኘት ነው ብለዋል። ከጥቂት ወራት በፊት የባሌ ብሔራዊ ፓርክን እንዲሁም ቀደም ሲል ሌሎች የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን መጎብኘታቸውን አስታውሰው በዛሬው እለት ደግሞ በጀጎል ዓለም አቀፍ ቅርስን ጨምሮ ሌሎችም የመስህብ ስፍራዎች መጎብኘታቸውን ገልጸዋል። በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ለዘማናት ተጠብቆ የቆየ ሃብት መሆኑን አንስተው አሁን ላይ ይበልጥ ለጎብኝዎች ምቹ እና ማራኪ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል። በሀረር ከተማ የተከናወኑ የኮሪደርና ሌሎች የከተማ ልማት ስራዎች የጀጎልን ዓለም አቀፍ ቅርስ ከመጠበቅም ባለፈ ለጎብኚው ውብ፣ ምቹና ማራኪ እንዲሆን አስችሎታል ብለዋል። በመሆኑም ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶችና እና የአለም አቀፍ ተቋማት የስራ ሃላፊዎች ቅርሱን የጎበኙት መሆኑን ገልጸዋል። በጉብኝቱ ከ40 በላይ እንግዶች መሳተፋቸውን ገልጸው፤ በቀጣይ የኢትዮጵያን ቅርሶችና የቱሪዝም ሃብቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ ጥሩ አጋጣሚ መሆኑን ተናግረዋል።
በድሬዳዋ የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ እየተደረጉ ነው
Nov 28, 2025 48
ድሬዳዋ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ ገበያን የማረጋጋት ሥራ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ ገለጹ። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን ምክንያት በማድረግ በአስተዳደሩ የተዘጋጀው የንግድ ባዛር ዛሬ በይፋ ተከፍቷል።   የንግድ ባዛሩን የከፈቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፈትህያ አደን፣ የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ እና ሌሎች አመራሮች ናቸው። በእዚህ ወቅት የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ እንደገለጹት፣ አስተዳደሩ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው። ገበያውን በማረጋጋት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግም የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎችን ከማቋቋም ባለፈ ከአጎራባች ክልሎችና በከተማዋ ካሉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በዛሬው ዕለት 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ የተከፈተው የንግድ ባዛር የዚሁ ገበያን የማረጋጋት ሥራ አካል መሆኑንም አመልክተዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር የንግድ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሚኖ ጠሃ በበኩላቸው፤ ምርትን በበቂ ደረጃ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ከማድረግ ጎን ለጎን በሸቀጦች ላይ ያልተገባ ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ጠቁመዋል።   የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን በተለያዩ አካባቢዎች ተደራሽ ከማድረግ ጎን ለጎን የሸማቾች ህብረት ሥራ ማህበራት የምርት አቅርቦታቸውን እንዲያሳድጉ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ቅናት በሚቆየው የንግድ ባዛር ላይ የንግድ ተቋማት እና ኢንተርፕራይዞች የተለያዩ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶቻቸውን ይዘው ቀርበዋል። ኢንተርፕራይዞቹና ተቋማቱ ባዛሩ ሸማቹን ከነጋዴዎች በቀጥታ በማገናኘት የገበያ ትስስር ከመፍጠር ባለፈ ለገበያ መረጋጋት ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።  
አሰብ የኢትዮጵያ ሉአላዊ ግዛት፤ ቀይ ባህር ደግሞ መውጫ መግቢያዋ ሆኖ ወደ ነባራዊ እውነታው ሊመለስ ይገባል
Nov 28, 2025 102
ሰመራ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ አሰብ የኢትዮጵያ ሉአላዊ ግዛት፤ ቀይ ባህር ደግሞ መውጫ መግቢያዋ ሆኖ ወደ ነባራዊ እውነታው ሊመለስ ይገባል ሲሉ የአፋር የሀገር ሽማግሌዎች ተናገሩ። ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ህጋዊ፣ ታሪካዊና መልከዓ ምድራዊ መብት የነበራት ቢሆንም ምክንያቱ እና ውሳኔ ሰጪው ባልታወቀበት ሁኔታ ከባለቤትነት እንድትርቅ ተደርጋ ለዓመታት ዘልቃለች። በዚህ ምክንያት ደግሞ ባለፉት 30 ዓመታት የባህር በር ባለቤትነት የሀገር ህልውና እና የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ መጥቷል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በትውልዱ ዘንድ ጥያቄ ሆኖ ከሶስት አስርተ ዓመታት በላይ የዘለቀ ሲሆን አሁን ላይ የህልውና ጉዳይ ሆኖ በሰላማዊ መንገድ የማግኘት ጥረት እየተደረገ ይገኛል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአፋር የሀገር ሽማግሌዎች አሰብ የኢትዮጵያ አካሏ፤ ቀይ ባህር ደግሞ መግቢያ መውጫ በሯ ሆኖ ለዘመናት ስለማገልገሉ በታሪክ የተዘመገበ እና ዓለም የሚያውቀው ሃቅ መሆኑን አንስተዋል። የአፋር ክልል ህዝብ ደግሞ ቀይ ባህር አቅራቢያው እያለ የተቆለፈበትና ከባህሩ የተገለለ ሆኖ በፍጹም ሊኖር የማይገባ በመሆኑ መብቱ ሊከበርለት ግድ ይላል ሲሉ አንስተዋል።   ከሀገር ሽማግሌዎቹ መካከል አቶ ጅብሪል ዓሊ እና አቶ ኡስማን ኢብራሂም፤ ኢትዮጵያ በአቅራቢያዋ ከሚገኘው ቀይ ባህር ተነጥላ ፈፅሞ ልትቀጥል አይገባም ብለዋል። በመሆኑም አሰብ የኢትዮጵያ ሉአላዊ ግዛት፤ ቀይ ባህር ደግሞ መውጫ መግቢያዋ ሆኖ ወደ ነባራዊ እውነታው ሊመለስ ይገባል ነው ያሉት። በየትኛውም መመዘኛ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ከቀይ ባህር መነጠል አይገባም በማለት አፅንኦት ሰጥተው ለመብታችን መከበር ህጋዊና መሰረታዊ ጥያቄያችን ይቀጥላል ብለዋል የሀገር ሽማግሌዎቹ።   የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በጋራ ከመጠቀምም ባለፈ የህይወት እና የደህንነት ጉዳይ በመሆኑ የግድ ምላሽ ሊሰጠው እንደሚገባ አቶ ኡስማን ተናግረዋል።   ሌላኛው የሀገር ሽማግሌ አቶ መሐመድ ሰኢድ፤ የአሰብ እና የቀይ ባህር ጉዳይ ታሪካዊና ህጋዊ መብታችን ሆኖ ሳለ በዝምታ መኖራችን ሁላችንንም ያስቆጨ ነው ብለዋል። አሁን ላይ ግን ትክክለኛ ምላሽ የሚሻ የሀገር ህልውና እና የትውልድ ጥያቄ በመሆኑ በአፋጣኝ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የስታንዳርድ ባንክ ተወካይ ጽህፈት ቤትን የሥራ ፈቃድ አደሰ
Nov 28, 2025 104
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተሻሻለው የባንክ ሥራ አዋጅ መሠረት በአዲስ አበባ ለሚገኘው የስታንዳርድ ባንክ ተወካይ ጽህፈት ቤት አዲስ የሥራ ፈቃድ በይፋ ሰጥቷል። በአዲሱ አዋጅ መሠረት የውጭ ባንኮች ተጠሪነት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሆኗል። በዚሁ መሠረት ከአሁን በኋላ የውጭ ባንኮች ተወካይ ጽህፈት ቤቶችን ፈቃድ የሚያድሰው እና አሠራራቸውንም በበላይነት የሚቆጣጠረው ብሔራዊ ባንኩ ይሆናል።   ይህ ተግባር እና ኃላፈነት ቀደም ሲል ለንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የተሰጠ እንደነበር ይታወቃል። ከአሁን በኋላ የሚመጡ አዲስ ማመልከቻዎችን መርምሮ ፈቃድ መስጠትም በአዲሱ አዋጅ መሠረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኃላፊነት መሆኑን ብሔራዊ ባንክ ገልጿል። የተወካይ ጽህፈት ቤቶች ሚና የገበያ ጥናት ማካሄድ፣ ማስተዋወቅ እና ትስስር መፍጠር ብቻ በመሆኑ፤ የባንክ አገልግሎት የመስጠት ስልጣን የሌላቸው መሆኑም ተመላክቷል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን አስቀርቶልናል-  ተገልጋዮች
Nov 28, 2025 102
ባሕር ዳር ፤ ሕዳር 19/2018(ኢዜአ) ፡- በባሕርዳር ከተማ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀደም ሲል ሲያጋጥማቸው የቆየውን እንግልት በማስቀረት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተገልጋዮች ገለጹ። በአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ለደንበኞች በተሰጠ የአገልግሎት እርካታ 95 በመቶ ማድረስ እንደተቻለ በተካሄደ ዳሰሳ ጥናት ማረጋገጥ መቻሉም ተገልጿል።   በአማራ ክልል ባሕርዳር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉዳይ ሲያስፈፅሙ ኢዜአ ያነጋገራቸው ሃይማኖት ይበልጣል እና ሰለሞን ውበት በሰጡት አስተያየት፤ በማዕከሉ ከእንግልት ነፃ የሆነ ፈጣን አገልግሎት ማግኘት እንደቻሉ ተናግረዋል። በማዕከሉ ከሰራተኞች አቀባበል ጀምሮ መልካም የሚባል አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።   ቀደም ሲል ማንኛውንም ዓይነት አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተቋማት በሚኬድበት ወቅት ፋይል ጠፋ በሚል ለመፈለግ ቀኑን ሙሉ ማሳለፍ ግድ እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ላይ በዘመናዊ አሰራር ችግሩን በመፍታት ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንደቻሉ አስረድተዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ቀደም ሲል ሲያጋጥማቸው የቆየውን እንግልት በማስቀረት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተገልጋዮቹ ገልጸዋል። የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው ፤ ሕዝብ የሚቸግራበችውን አገልግሎቶች በመለየት የማዘመን ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።   በባሕር ዳር ከተማ የተጀመረው የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ12 ተቋማት 92 አገልግሎቶችን ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ አሁን ላይ በዘጠኝ ተቋማት 48 አገልግሎቶችን መስጠት እንደተቻለም አስታውቀዋል። የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ባንችዓምላክ ገብረማርያም፤ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት አስተዳደር ሪፎርምና የዲጂታል ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ አካል ሆኖ እየተተገበረ ነው ብለዋል።   የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጡ የመንግስትንና የሕዝብን ትስስርን ይበልጥ በማጠናከር የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታተ በጥናት ተለይቶ የተገባበት ተግባር መሆኑን አንስተዋል።   በክልሉ አራት የፌደራልና አስር የክልል ተቋማት 54 አገልግሎቶችን እየሰጡ ሲሆን፤ በአንድ ወር ተኩል ጊዜ ውስጥ ከ10 ሺህ 400 በላይ ደንበኞችን ማስተናገድ እንደተቻለም አስረድተዋል። ከደንበኞች በተደረገ የዳሰሳ ጥናትም የአገልግሎት እርካታውን 95 በመቶ ማድረስ መቻሉም ተረጋግጧል ብለዋል።
ቴክኖሎጂን በመጠቀም ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 28, 2025 99
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ገለጸ፡፡ የመስሪያ ቤቱ ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ መስሪያ ቤቱ የሀገሪቱን ውስን ሀብትና ንብረት ከብክነት ለማዳን እንዲሁም ብልሹ አሠራሮችን የመከላከል ተልዕኮውን አጠናክሮ መቀጠሉንም ተናግረዋል፡፡ በዚህም የፌዴራል መስሪያ ቤቶች የተበጀተላቸውን በጀት ለታለመለት ዓላማ ማዋላቸውን ኦዲት በማድረግ በማረጋገጥ ላይ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በዚህም ፋይናንሻል ኦዲት፣ ክዋኔ ኦዲት፣ ልዩ ኦዲትን ጨምሮ በሌሎችም ጉዳዮች የኦዲት ስራ በመከናወን ላይ እንሚገኙ ገልጸዋል፡፡ መስሪያ ቤቱ ተጠያቂነትን ለማስፈንም ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከፍትህ ሚኒስቴር እና ከስነ ምግብርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ዋና ኦዲተሯ ጠቅሰዋል። እንደ ኦዲት ግኝቱም መሸለም የሚገባቸው ተቋማት የሚሸለሙበትና ተጠያቂ የሚሆኑ ተቋማት የሚጠየቁበት አሠራር መዘርጋቱን ተናግረዋል፡፡ በኦዲት ግኝቱ መሠረት ከኃላፊነታቸው የተነሱና ተጠያቂ የሆኑ አመራሮች መኖራቸውን ለአብነት አንስተው፤ ከለውጡ ወዲህ የክዋኔ ኦዲት ቁጥርና የክትትል አቅም እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመዋል። በቴክኖሎጂ የታገዘ ዲጂታል አሠራር ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲኖር፣ የገንዘብ ንክኪን ለማስቀረት እንዲሁም የአሠራር ስርዓትን በማዘመን ሙስናን ለመከላከል ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። ይህም ሙስናና ብልሹ አሠራሮችን ለመቆጣጠር ትልቅ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ጠቁመው፤ ወቅቱ የሚፈልገውና ዓለም እየሄደበት ያለው አቅጣጫ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ መስሪያ ቤቱም አሠራሩን ለማዘመን ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ስልጠናው በፈጠራ የታገዘ ተግባራትን ለማከናወን አግዞናል - የኮደርስ ሰልጣኞች
Nov 28, 2025 63
ወልዲያ፤ ሕዳር 19/2018(ኢዜአ)፡- በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የተመቻቸላቸውን ዕድል በመጠቀም በፈጠራ የታገዘ ተግባራትን ለማከናወን እንዳገዛቸው በሰሜን ወሎ ዞን የኮደርስ ሰልጣኞች ገለጹ። የ "አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ" ስልጠና ኢንሼቲቭ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረገ የዲጂታል ክሕሎት ማሳደጊያ መረሃ ግብር ነው። "ትውልድ ይማር፣ ይሰልጥን ፣ ከዓለም ጋር ይፎካከር" በሚል እሳቤ መርሃ ግብሩ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ ሲሆኑ፤ ከእነዚህም በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ ዞን ይገኝበታል። በሰሜን ወሎ ዞን ባለፉት አራት ወራት ከሁለት ሺህ በላይ ወጣቶችና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች የኮደርስ ስልጠናን በብቃት በማጠናቀቅ የማረጋገጫ ሰርቲፊኬት መውሰዳቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል። ስልጠናውን ካጠናቀቁት መካከል የዞኑ የመንግሰት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ባለሙያ የሆኑት ታደሰ አብዬ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ ስልጠናው በፈጠራ የታገዘ ተግባራትን ለማከናወን አቅም ፈጥሮልኛል ብለዋል። በተለይ የኮምፒውተር ስራን አቅልሎ ለመስራትና ከወረቀት የተላቀቀ ዲጂታላይዜሽን አሰራርን መተግበር የሚያስችል እውቀት እንዳገኙበት ተናግረዋል። የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የአገልግሎት አስጣጥን የሚያቀላጥፍ ነው ያሉት ደግሞ ሌላው ሰልጣኝ አቶ ሰለሞን አሰፋ ናቸው።   ስልጠናው ሁለት ወራት እንደወሰደባቸው ጠቅሰው፤ ቀደም ሲል ያላወቅኳቸውን የመረጃ አያያዝና ሌሎች ዕውቀቶችን እንዳገኝ አግዞኛል ብለዋል። ስልጠናው ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠትና የመልካም አስተዳደርን ማስፈን የሚያስችል በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመልክተዋል። በሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ አማኑኤል ሮብሶ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሕብረተሰቡን በተለይም ወጣቱን በኮደርስ ስልጠና ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው። የመርሃ ግብሩ ዓላማ ወጣቱ ትውልድ እንዲሁም አመራሩና ሠራተኛው በዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ መሳተፍ የሚያስችላቸውን የዲጂታል ክህሎት እንዲኖራቸው ለማመቻቸት እንደሆነ ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱም ከ25ሺህ በላይ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በኮደርስ ለማሰልጠን ታቅዶ በተደረገ ጥረት በአራት ወራት ውስጥ ከሁለት ሺህ በላይ ማሰልጠን መቻሉን አስታውቀዋል። በፕሮግራሚንግ ልማት፣ በዳታ ሳይንስ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ከህሎትን ለማስጨበጥ የተሰጠውን ስልጠና ላጠናቀቁ ሰርትፍኬት እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል። በቀሪ ወራትም የስልጠና ማዕከላትን በማስፋት የታቀደውን ለማሳካት ሁሉን አቀፍ ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል። ለስልጠናው ስኬት በዞንና በወረዳ የሚገኙ የአይ ሲቲ ማዕከላት፣ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ አይሲቲ ማዕከላት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑም ተመልክቷል።
በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ምሕዳሩን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ 
Nov 27, 2025 184
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ምሕዳሩን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል አስታወቁ። "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ሲካሄድ የቆየው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት ዛሬ ተጠናቋል። ተቀማጭነቱን አሜሪካን ሀገር ያደረገው ግሎባል ኢንተርፕርነርሺፕ ኔትወርክ፤ ኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ ባዘጋጀቻቸው ኹነቶች ከ200 ሀገራት ጋር ተወዳድራ አንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጿል።   የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢንተርፕርነር ምህዳር ግንባታ ላይ የተከናወኑ ስራዎች በዘርፉ ውጤት እንዲመዘገብ አድርጓል። በአሁኑ ወቅት በኢንተርፕርነር ዘርፉ ላይ የተገኘው ስኬት የኢትዮጵያን አዲስ መልክና እድገት ለማስተዋወቅ የሚረዱ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ውድድር በማድረግ ከዓለም ስምንተኛ ከአፍሪካ ደግሞ ሁለተኛ በመሆን አጠናቅቃ እንደነበርም አስታውሰዋል። በዘንድሮው ዓመትም በርካታ ተቋማት በመደመር እሳቤ በዘርፉ በትብብር መስራታቸው ኢትዮጵያ ቀዳሚውን ስፍራ በመያዝ ውድድሩን እንድታጠናቅቅ አድርጓል ነው ያሉት።   በአጭር ጊዜ ውስጥ የኢንተርፕርነር ዘርፍ ምህዳርን በማስፋት ለውጥ እንዲመጣ ማድረግ ተችሏል ያሉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ፤ በቅንጅት ከተሰራ የኢትዮጵያን እድገት ለማሳካት እንደማያዳግትም አመላካች መሆኑን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በውድድሩ ያስመዘገበችው ውጤት ኢንቨስትመንትን ከመሳብ ባሻገር ችግር ፈቺ ኢንተርፕርነሮችን እና በዘርፉ ምርምር የሚያደርጉ አካላትን ለማፍራት እንደሚረዳ አብራርተዋል፤ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሀሰን ሁሴን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በዘንድሮው ዓመት ኢንተርፕነር ዘርፉን ለመለወጥ በጋራ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት አምጥተዋል። ይህንን ጥረት በማጠናከርም በቀጣይ በተለይ የዘርፉን ምህዳር የማስፋት ስራን ስኬታማ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸውም ነው ጥሪያቸውን ያስተላለፉት ።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል 
Nov 28, 2025 112
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከረፋዱ 4 ሰዓት ላይ ሃዋሳ ከተማ ከሲዳማ ቡና በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሃዋሳ ከተማ በሊጉ ካደረጋቸው ስምንት ጨዋታዎች መካከል ስድስቱን ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። 16 ግቦችን በጨዋታዎቹ ላይ ሲያስቆጥር ሰባት ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ18 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሲዳማ ቡና በበኩሉ በውድድር ዓመቱ ሰባት ጨዋታዎችን አድርጎ ሁለት ጊዜ ድል ሲቀናው በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። ሶስት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥቷል። ሰባት ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ አምስት ግቦች ተቆጥረውበታል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ሲዳማ ቡና በዘጠኝ ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃን ይዟል። በሌላኛው መርሃ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከይርጋጨፌ ቡና ከቀኑ 7 ሰዓት በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ ባካሄዳቸው ስምንት ጨዋታዎች ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ አምስት ጊዜ ተሸንፏል። ስምንት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 13 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በዘጠኝ ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። አዲስ አዳጊው ይርጋጨፌ ቡና በበኩሉ ከሰባት የሊጉ ጨዋታዎች መካከል ሁለቱን ሲያሸንፍ በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ሽንፈትን አስተናግዷል። በአራት ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ ሶስት ግቦች ሲያስቆጥር ስድስት ግቦችን አስተናግዷል። ይርጋጨፌ ቡና በ10 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።   የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት መርሃ ግብር እስከ ሕዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ24 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። ባህር ዳር ከተማ እና አዲስ አበባ ከተማ 13ኛ እና 14ኛ ደረጃን ይዘው ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛሉ። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን የኢትዮ ኤሌክትሪኳ ዳግማዊት ሰለሞን በ16 ግቦች ትመራለች። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ መሳይ ተመስገን በአምስት ግቦች ትከተላለች።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመቀሌ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና ከአርባምንጭ ከተማ ያደረጓቸው ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ
Nov 27, 2025 133
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 18/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ስምንተኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ተካሄደዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ መቀሌ 70 እንደርታ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ኪቲካ ጅማ እና ሱሌይማን ሀሚድ ለመቀሌ 70 እንደርታ ግቦቹን አስቆጥረዋል። አዲስ ግደይ እና ኤፍሬም ሌጋሞ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጎሎቹን ከመረብ ላይ ያሳረፉ ተጫዋቾች ናቸው።   መቀሌ 70 እንደርታ በሶስት ነጥብ 19ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ እስከ አሁን በሊጉ ምንም ጨዋታ አላሸነፈም። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ10 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሀዲያ ሆሳዕና ከአርባምንጭ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። እዮብ አለማየሁ ለሀዲያ ሆሳዕና እና ታምራት እያሱ ለአርባምንጭ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሀድያ ሆሳዕና በሰባት ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።   አርባምንጭ ከተማ በአራት ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቡድኑ በውድድር ዓመቱ አንድም ጨዋታ ማሸነፍ አልቻለም። ዛሬ አስቀድሞ በተደረገ የሊጉ ጨዋታ ምድረገነት ሽሬ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የሰባተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የስምንተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከሕዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤን ለማስተናገድ መመረጥ የታዳሽ ኃይል ልማት ቁርጠኝነቷን የሚያረጋግጥ ነው
Nov 28, 2025 99
አዲስ አበባ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት(COP-32) ጉባኤ ለማስተናገድ መመረጥ ለታዳሽ ኃይል ልማት ትግበራ ቁርጠኝነቷን የሚያረጋግጥ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) ገለጹ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ በሁሉም የታዳሽ ኃይል አማራጭ ዕምቅ የመልማት አቅም አላት። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ግንባታም የውሃ፣ የፀሐይ፣ የነፋስ፣ ጂኦተርማልና መሰል የኃይል አማራጮች ወሳኝ ሚና እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን በፀሐይ ኃይል የኤሌክትሪክ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል ባልተዳረሰባቸው የገጠር መንደሮችና ከተሞች የፀሐይ ኃይል ተጠቃሚነት ለማሳደግ ከልማት አጋሮች ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት ስኬትም የካርቦን ልቀትና የአየር ንብረት ለውጥ ስጋትን በመቀነስ ዓለም አቀፍ እውቅና እያስቸራት መሆኑን አብራርተዋል።   የበለጸጉ ሀገራት ዕድገታቸውን ለማረጋገጥ የተጓዙበት መንገድ በካይ ጋዞችን በመጠቀም በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ዓለምን ዋጋ እያስከፈሉ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በኢትዮጵያ የሚገነቡ የታዳሽ ኃይል አማራጭ መሠረተ ልማቶችም በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ እየተፈተነ ለሚገኘው ዓለም ከፍተኛ ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰዋል። የታዳሽ ኃይል መሠረተ ልማት ግንባታም የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ወሳኝ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል አማራጭ ልማት ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን በማጠናከር ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎችን የምታስተናግድበትን ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። በብራዚል በተካሄደው መድረክ ኢትዮጵያ ኮፕ-32 ጉባኤን ለማስተናገድ ስትመረጥ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ያስመዘገበችው ስኬት ተጠቃሽ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ-32 ጉባኤን ለማስተናገድ መመረጧ በታዳሽ ኃይል አማራጭ፣ አረንጓዴ ዐሻራ እና በታዳሽ ኃይል ልማት ላስመዘገበችው ስኬት ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም የኢትዮጵያ የውሃ ሃብቶችን ደኅንነት በመጠበቅና የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከደለል በመታደግ ወሳኝ ድርሻ እየተጫወተ ነው ብለዋል። በብራዚል ቤለም በተካሄደው 30ኛ ጉባኤ ላይ ከሁለት ዓመታት በኋላ የሚካሄደውን 32ኛ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ (COP-32) ኢትዮጵያ እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለተተከሉ ችግኞች በተደረገ እንክብካቤ የጽድቀት መጠንን ማሳደግ ተችሏል
Nov 28, 2025 65
ደብረ ማርቆስ ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ባለፈው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ለተተከለው ችግኝ የእንክብካቤ ስራ እየተካሄደ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የተፈጥሮ ሃብት ቡድን መሪ አቶ ንጉሴ ሽመልስ ለኢዜአ እንደገለጹት የሚተከሉ ችግኞችን የጽድቀት መጠን በመጨመር የደን ሽፋኑን ለማሳደግ የእንክብካቤ ስራ እየተሰራ ነው።   በዚህም ባሳለፍነው ክረምት ከተተከለው ከ219 ሚሊዮን በላይ ችግኝ ውስጥ 87 በመቶ የሚሆነው መጽደቅ መቻሉን ገልጸዋል። በዚህ ዓመት የተመዘገበው የችግኝ ጽድቀት መጠን ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከሰባት በመቶ በላይ ብልጫ እንዳለው ተመልክቷል። ከ500 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ችግኞችን በማረም፣ በመኮትኮት፣ ውሃ በማጠጣትና ከእንስሳት ንክኪ ነጻ በማድረግ በተሰራው ስራ የጽድቀት መጠኑ እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል። በዞኑ የአነደድ ወረዳ የጉዳለማ ቀበሌ ነዋሪ አቶ መንግስቱ ስሜነህ እንዳሉት፤ በአረንጓዴ ልማቱ የተተከሉ ችግኞች የመሬታቸውን ለምነት በመጨመር ምርታማነታቸው እንዲያድግ እያደረገ ነው። ይሄን በመገንዘብም ዘንድሮ የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ ለማድረግ በመጠበቅና በመንከባከብ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።   የደጀን ወረዳ የሽንቡሪ ቀበሌ ነዋሪ አቶ አንዷለም አምሳሉ በበኩላቸው ፤ በየዓመቱ የሚተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ የጽድቀት መጠኑ እንዲጨምር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የተተከሉ ችግኞች የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ ማድረጋቸውን ጠቁመው በቀጣይም ችግኞችን የመትከልና የመንከባከብ ስራን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ የተሰሩ ተግባራት የዞኑን የደን ሽፋን ባለፈው ዓመት ከነበረበት ከ17 ነጥብ 4 በመቶ ወደ 18 ነጥብ 1 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ኢትዮጵያ የኮፕ-32 ጉባኤን እንድታዘጋጅ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ለሰራቻቸው ውጤታማ ሥራዎች የተሰጠ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ነው 
Nov 27, 2025 149
አዲስ አበባ፤ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የኮፕ-32 ጉባኤን እንድታዘጋጅ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ለሰራቻቸው ውጤታማ ሥራዎች ዳግም የተሰጠ ዓለም አቀፍ ዕውቅና መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ዋና ዋና የዲፕሎማሲ ስራዎችን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ ጉባኤውን እንድታዘጋጅ መመረጧ በአረንጓዴ ልማት፣ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ማበረታቻ፣ በአረንጓዴ ዐሻራ እና መሰል የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራዎች ላይ እያከናወነች ለሚገኙ ተግባራት የተሰጠ እውቅና ነው። ኢትዮጵያ የኮፕ-32 አስተናጋጅ ሆና መመረጧ በዲፕሎማሲው መድረክ ያላት ተሰሚነት ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ መሆኑንም ጠቁመዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ-32) ተወካይ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውንም ተናግረዋል። ጉባኤው ኢትዮጵያ አጀንዳዎቿን ለዓለም የምታስተዋውቅበት ትልቅ መድረክ እንደሚሆንም አምባሳደሩ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የቡድን-20 ጉባኤ ላይ በመሳተፍ የዲፕሎማሲ ስኬት ማስመዝገቧን ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ባደረጉት ንግግር የአፍሪካን ሁነኛ አጀንዳዎችን ማንጸባረቃቸውንም አስታውሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከተመድ፣ ከዓለም ባንክ፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክ፣ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) እና ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች ጋር ውጤታማ የጎንዮሽ ውይይቶችን ማድረጋቸውንና በርካታ ስምምነቶች መፈጸማቸውን ገልጸዋል። የማሌዥያና የሲንጋፖር ሀገራት መሪዎች የሥራ ጉብኝት ኢትዮጵያ ካላት ሁለገብ የልማት ጉዞ አንፃር ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከሀገራቱ ጋር በነዳጅ፣ በታዳሽ ኃይል፣ በግብርና፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በስማርት ከተማ ልማት እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ስምምነት መደረጉን አስታውቀዋል። በተሰሩ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራዎች ምክንያት የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲያቸውን በአዲስ አበባ የከፈቱ ሲሆን፣ ሌሎችም ለመክፈት መወሰናቸው በመግለጫው ተመላክቷል። በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ መስክ የተከናወኑ ተግባራትን በተመለከተም፤ በሳውዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ወደ 23 ሺህ የሚጠጉ ዜጎችን በቅርቡ ወደ ሀገር መመለስ እንደተቻለ ተመላክቷል። ኢትዮጵያ በብራዚል ቤለም በተካሄደው የዓለም የአየር ንብረት (COP-30) ጉባኤ ላይ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት (COP-32) ጉባኤ ለማስተናገድ መመረጧ ይታወቃል።  
መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉና ለዱር እንስሳት ሀብት የሰጠው ትኩረት ለዱር እንስሳት ጥበቃ ምቹ መደላድል ፈጥሯል
Nov 27, 2025 123
አዲስ አበባ፤ህዳር 18/2018(ኢዜአ)፦መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉና ለዱር እንስሳት ሀብት የሰጠው ትኩረት ለዱር እንስሳት ጥበቃና ባለስልጣኑ ለሚያከናውነው ተግባር ምቹ መደላድል መፍጠሩን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ ገለፁ። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ በትናንትናው እለት በለንደን በተካሄደው በአፍሪካ በብዝሃ ህይወት ጥበቃ የሚሰጠው ፕሪንስ ዊሊያም አዋርድ የ2025 አሸናፊ ሆነዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አሸናፊ የሆኑት ተስክ ጥበቃ ሽልማት 2025 በተዘጋጀው በአፍሪካ በብዝሃ ህይወት ጥበቃ የላቀ ድርሻና አስተዋፅኦ ላበረከቱ ሰዎች በሚሰጠው የህይወት ዘመን አበርክቶ ሽልማት ዘርፍ ነው። አቶ ኩመራ በዱር እንስሳት ጥበቃ ዘርፍ ከባለሙያነት እስከ ዋና ዳይሬክተርነት ከ30 ዓመት በላይ ያገለገሉ ሲሆን በዘርፉ በተለያዩ የጥናት እና ምርምር እንዲሁም የአስተዳደር ሥራዎች ላይ ያበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦ ሽልማቱን ለማሸነፍ አስችሏቸዋል። የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ እንዳሉት ባለስልጣኑ የዱር እንስሳትና መኖሪያ አካባቢያቸው በአግባቡ ተጠብቆና ለምቶ በዘላቂነት ጥቅም ላይ ለማዋል እየሰራ ይገኛል። የጥበቃ ቦታዎችን በጥናት ለይቶ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ማቋቋም እንዲሁም የአስተዳደር ስርዓት ዘርግቶ በአግባቡ እንዲጠበቁና እንዲለሙ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ባለስልጣኑ የዱር እንስሳት መጠለያ፣ የስፖርታዊ አደን የሚካሄድባቸው ጥበቃ ቦታዎችን ጨምሮ በተለያዩ ምድብ ያሉ የጥበቃ ቦታዎች በአግባቡ እንዲጠበቁ የማድረግ ስራም ያከናውናል ነው ያሉት። የጥበቃ ስራዎችን ከክልሎች፣ከማህበረሰቡ የሚመለከታቸው አካላት ጋር ከመስራት ባለፈ በዱር እንስሳት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል ከአገራት ጋር በመተባበር እንደሚሰራም ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉና ለዱር እንስሳት ሀብት የሰጠው ትኩረት ለዱር እንስሳት ጥበቃና ባለስልጣኑ ለሚያከናውነው ተግባር ምቹ መደላድል መፍጠሩን ጠቁመዋል። ያገኙት ሽልማትም ዘርፉ የተሰጠው ትኩረት አለም አቀፍ እይታ እንዲያገኝ ለማስቻሉ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። ሽልማቱ ለዱር እንስሳት ጥበቃ የበለጠ ድምፅ ለመሆን፣ ህፃናት ለተፈጥሮ ሀብት ያላቸውን ተቆርቋሪነት ለማሳደግና የተፈጥሮ ሀብት አርበኛ የሆኑት ሬንጀሮች ማህበር የበለጠ ለማጠናከር እንዲተጉ የቤት ስራ የሚሰጥ ነው ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 402
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 342
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል።   ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል።   ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ለሱዳን ግጭት ዓለም አቀፍ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል- ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
Nov 19, 2025 448
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የሱዳን ግጭት ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቀናጀ ምላሽ እንዲሰጥ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ያዘጋጀው ሁለተኛ የሱዳን የልዩ ልዑኮች ፎረም ዛሬ በጅቡቲ ተካሄዷል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ተዋንያን ተሳትፈዋል። ፎረሙ በሱዳን ላለው ቀውስ የተቀናጀ መልስ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።   የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር የሱዳን ሰላም በሱዳናውያን የሚመራ፣ ቀጣናዊ ትብብር የተረጋገጠበት እና ዓለም በአንድ ድምጽ የሚደግፈው ሊሆን እንደሚገባ አመልክተዋል። በሱዳን ያለውን ግጭት ለማስቆም፣ ንጹሃን ዜጎችን ለመጠበቅ እና የኢጋድ ቀጣናን የተረጋጋ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ዋና ፀሐፊው ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን በሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደረስ፣ የሰብዓዊ እርዳታ መተላለፊያ እንዲከፈት እና ተአማኒነት ያለው የስልጣን ሽግግር እንዲኖር በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። ኢጋድ ሱዳናውያን በሀገራቸው ሰላም እና ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ክብራቸው እንዲጠበቅ ያላቸው መሻት እንዲሳካ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በመረጃው አመልክቷል።
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 747
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል።   የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 96
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል።   የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው።   ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።  
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 525
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 551
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 611
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2468
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2562
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3456
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3541
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 1725
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1151
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6969
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5448
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57200
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52260
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32957
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30469
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26516
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25221
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24819
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 24806
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57200
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52260
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 32957
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30469
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በቅሎ ወለደች
Nov 28, 2025 311
ቦንጋ፤ሕዳር 19/2017(ኢዜአ)፦ዛሬ ከወደ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ያልተለመደ ክስተት ታይቷል። ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም እንዲሉ ጉዳዩ እንዲህ ነው፤ በክልሉ ዳውሮ ዞን ዛባ ጋዞ ወረዳ ያማላ ቦካ ቀበሌ አንዲት በቅሎ ወልዳለች። መውለድ ከማይችሉ እንስሳት ተርታ የምትመደበው በቅሎ የመውለዷ ነገር አዲስ ክስተት ሆኗል። ጉዳዩን በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የበቅሎዋ ባለቤት የሆኑት አቶ ነጋሽ በተላ በተፈጠረው ነገር እጅጉን መደናገጣቸውን ገልጸዋል። በቅሎ በተፈጥሮ እንደማትወልድ የሚታወቅ ቢሆንም በቤታቸው የተከሰተውን ነገር ማመን እንደከበዳቸው ነው የተናገሩት። ከወትሮ የተለየ ነገር እንዳላሳየችና ትላንትና ማታ ባልጠበቁት ሁኔታ ወልዳ መመልከታቸውን አቶ ነጋኝ አውስተው፤ በቅሎዋ ከወለደች በኋላ ምንም አዲስ ነገር እንዳላሳየችም አስረድተዋል። በዛባ ገዞ ወረዳ የማላ ቦካ ቀበሌ የእንስሳት ባለሙያው አቶ ደረጀ ደስታ ፤ ክስተቱ ከሳይንስና ከተፈጥሮም የሚቃረን ለማመን የሚከብድ መሆኑን ገልጸዋል። የተወለደው ፍጡር የፈረስ ቅርፅ ያለው ፣ ገና ፀጉር ያላበቀለና ቀኑ ያልደረሰ እንደሆነም አስረድተዋል። ሲወለድም የሞተ ሲሆን በቅሎዋ አሁን ላይ በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሆነችና ምንም የተለየ ምልክት እንዳላሳየችም ነው ለኢዜአ የገለጹት። ይህን አዲስ ክስተት ከተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል የአቶ ነጋኝ ጎረቤት የሆኑት አቶ ባሳ ፈልታሞ፥ይህ ነገር ለማመን የሚከብድ ክስተት ነው፤ ከዚህ በፊት እንዲህ ዓይነት ነገር ሰምቼም ሆነ አይቼም አላውቅም ሲሉ ገልጸዋል።
ድንበር ተሻጋሪው የኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር ወዳጅነት
Nov 27, 2025 152
ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1969 ነው። ሀገራቱ በተለያዩ ክፍለ አህጉራት የሚገኙ ቢሆንም ርቀት ሳይገድባቸው በዲፕሎሲ እና ኢኮኖሚ መስኮች ያላቸውን ትብብር ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ለማስፋት እየሰሩም ይገኛሉ። ሲንጋፖር በፍጥነት እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፣ ስትራቴጂካዊ ስፍራና ከፍተኛ የህዝብ ብዛት በመጠቀም ትስስሯን የማጎልበት ጠንካራ ፍላጎት አሳይታለች። እ.አ.አ በ2017 የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና የሲንጋፖር የሕብረት ስራ ኢንተርፕራይዝ የተፈራረሙት የጋራ መግባቢያ ስምምነት የዚሁ ማሳያ ነው። ስምምነቱ ሲንጋፖር በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማትና የንግድ ስራ ምቹነት ሪፎርሞች ልምዷን የምታካፍልበት ነው። ሎጅስቲክስ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ግብርና ማቀነባበሪያ፣ ማዕድንና ቱሪዝም ትብብራቸውን ለማጠናከር የጋራ ስምምነት ላይ ከደረሱባቸው መስኮች መከላከል ይጠቀሳሉ። ኢትዮጵያ ለሲንጋፖር የአፍሪካ የኢንቨስትመንት መግቢያ በር፣ ሲንጋፖር ለኢትዮጵያ የእስያ መግቢያ በር ናቸው ማለት ይቻላል። ሁለቱ ሀገራት በተደጋጋሚ የንግድ እና ኢንቨስትመንትን ጨምሮ አጠቃላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል። ሌላኛው የሀገራቱ የትብብር መስክ አቪዬሽን ነው። የኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር አየር መንገዶች እ.አ.አ በ2012 የአየር አገልግሎት ትብብር ስምምነት መፈራረማቸው ይታወቃል። ስምምነቱ የመንገደኞችና ካርጎ በረራዎችን እንዲሁም የትራንስፖርት ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችል ነው። የአየር አገልግሎት ስምምነቱ በምስራቅ አፍሪካና በደቡብ ምስራቅ እስያ መካከል በጉዞ፣ በካርጎ ንግድ እና ሎጅስቲክስ ያለውን ትብብር ለማጎልበት ያስችላል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እ.አ.አ በ2024 በሲንጋፖር ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል። ጉብኝቱ ሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩበት 55ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር የተገጣጠመ ነበር። በጉብኝቱ ወቅት ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ ሀገራቱ በመደበኛነት የሁለትዮሽ ምክክር እንዲያደርጉ፣ በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ነው። ሲንጋፖር በኢትዮጵያ ኤምባሲ እንደምትከፍት ይፋ አድርጋለች። የሲንጋፖር ውሳኔ ከኢትዮጵያ አልፎም ከቀጣናው ጋር በትብብር ለመስራት ያላትን የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሆኗል።   የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ በቅርቡ በአዲስ አበባ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን ትብብራቸው ዙሪያ መክረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ውይይቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል ያለውን ግንኙነት ለጋራ ነጋችን ወሳኝ በሆኑ መስኮች በጋራ ለመሥራት በምናደርገው ጥረት ውስጥ አንድ ጠቃሚ ርምጃ ነው ሲሉም ገልጸውታል። በተለይም በክሂሎት ልማት እና የካርበን ብድር ትብብር ላይ የተፈረሙት የመግባቢያ ስምምነቶች ጽኑ እና ለነገው ገበያ ዝግጁ የሆኑ ሠራተኞችን ለማፍራት ብሎም በአየር ንብረት ጥበቃ ረገድ ዘላቂ፣ ዝቅተኛ ካርበን የሚያወጣ እድገት ለማረጋገጥ ያለንን የጋራ አቋም ያንጸባርቃል ነው ያሉት። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም በላቀ ተግባራዊ ትብብር ንግድ እና ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት፣ ዘመናዊ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስን በማልማት፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በገንዘብ ልውውጥ ቴክኖሎጂ፣ ሳይበር ደኅንነትና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለንን ትብብር ለመጠቀም እጅግ ሰፊ አቅም አለ ነው ያሉት። ሁለቱም መሪዎች በጉብኝቱ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማላቅ፣ ተቋማዊ መስተጋብርን ለማጠናክር ብሎም የወል ቅድሚያዎቻቸውን ከፍ አድርጎ ለመከወን መንገዶችን እንደተመለከቱበትም ተናግረዋል። ሲንጋፖር በኢትዮጵያ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗ ከኢትዮጵያ ባለፈ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትስስር ማጎልበት የሚያስችላትን ማዕቀፍ እንደሚፈጥር የገለጹት ደግሞ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ ናቸው። ከዚህ በፊት የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ኢትዮጵያን የጎበኙት እ.አ.አ በ1964 እንደነበር አስታውሰው የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከር እና ለሲንጋፖር አዳዲስ የንግድ በሮች መክፈት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን አመልክተዋል። አስተዳደር፣ ትምህርት እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ከሚፈልጉባቸው መስኮች መካከል እንደሚጠቀሱ አንስተው የሀገራቱ መሪዎቹ በተገኙበት ከቁልፍ የጋራ ፍላጎቶቻችን ጋር የሚጣጣሙ የክህሎቶች ልማትና የካርቦን ገበያ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራረመናል ብለዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት ተናግረዋል። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖር እና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድል በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር የቅርብ ጊዜ ውይይቶችና የጉብኝት ልውውጦች ሀገራቱ በጋራ ለመልማትና ለማደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት ትብብር በአፍሪካ እና በደቡብ ምስራቅ እስያ መካከል እንደ ድልድይ ሆኖ የሚያገለግል ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም