ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የጎንደር ሁለተኛው የሥልጣኔ ዘመን ተበሠረ- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Nov 7, 2025 19
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):- የጎንደር ሁለተኛው የሥልጣኔ ዘመን ተበሠረ ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ የፋሲል ግንብ ለአራት መቶ ዓመታት ያህል የሚንከባከበው አጥቶ የእርጅና እድሜው ላይ ደርሶ ሞቱን ነበር የሚጠብቀው ሲሉ አስፍረዋል። በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አመራርና ክትትል እንደ ንሥር ታድሶ ተነሣ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአዘዞ እስከ ፒያሳ ያለው የጎንደር መንገድ ግራና ቀኙ እየተስተካከለ እና እያማረ ዳግም እየተወለደ ነው ያውም ውበት፣ ጥቅምና ምቾት ጨምሮ ብለዋል። ተጀምሮ ያለማለቅና ቆሞ የመቅረት መተረቻ የሆነው መገጭ ዛሬ ታሪኩ ተቀየረ፤ ወድቆ የመነሣት፣ ደክሞ የመበርታት ምሳሌ ሆነ ሲሉም ገልጸዋል። ወንዙ ተቀለበሰ፤አንዱን ወሳኝ ምእራፍ ተሻገረ፤እነሆ የጎንደር ሁለተኛው የሥልጣኔ ዘመን በዚህ ሰሞን ተበሠረ ሲሉም ነው የገለጹት።
የጋራ ትርክትን በመገንባት የሀገርን ሰላምና አንድነት ለማጽናት የድርሻችንን እንወጣለን-የኪነ ጥበብ እና የሚዲያ ባለሙያዎች
Nov 7, 2025 28
ደሴ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):-የጋራ ትርክትን በመገንባት የሀገርን ሰላምና አንድነት ለማጽናት በሚደረገው ጥረት የድርሻንን እንወጣለን ሲሉ የኪነ ጥበብ እና የሚዲያ ባለሙያዎች ተናገሩ። የደሴ ከተማ አስተዳደር "ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ከኪነ ጥበብ ፣ ከሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና ከማህበረሰብ አንቂዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሄዷል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል ጋሻው ገብሬ በሰጠው አስተያየት እንደገለጸው፣ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የጋራ ትርክት መገንባት ላይ መስራት ከሁሉም ይጠበቃል። ለዚህም የኪነ ጥበብ ሙያውን ተጠቅሞ ህብረተሰቡን የሚያስተምሩ በጋራ ትርክት ላይ ያጠነጠኑ ስራዎችን በማቅረብ ሰላምን ለማጽናት በሚደረገው ጥረት የድርሻውን እንደሚወጣ ተናግሯል። የወሎ ባህል ቡድን ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሳሙኤል በላይ በበኩሉ፣ የጋራ ትርክትን የሚያጎለብቱና ሰላምን የሚያጸኑ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ገልጿል። በዚህም በኪነ ጥበብ ስራዎች ባህሎችን በማስተዋወቅ፣ ሰላምን በመስበክ፣ የእርስ በእርስ ግንኙነቶችን በሚያጠናክሩ ስራዎች ላይ በመሳተፍ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አክሏል። የኪነ ጥበብ ባለሙያዋ እንግዳወርቅ ካሳሁን ፤ጥበብ እያዝናናችና እያዋዛች ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለመፍጠር፣ ሰላምን ለማጽናትና የልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ያላትን አቅም ተጠቅመን እንሰራለን ብላለች። የደሴ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትግስት አበበ በበኩላቸው፣ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ዘርፉ ለሀገር ሰላም፣ ልማትና አንድነት በቁርጠኝነት መስራት አለበት ብለዋል። በዚህም የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የመረዳዳት፣ የመጠያየቅና የአብሮነት ልምዶች እንዲጎለብቱ እያደረጉ ያለውን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰኢድ ካሳው በበኩላቸው፣ ለከተማዋ ዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም በየደረጃው ውይይቶች እየተካሄዱ መሆኑን ጠቁመው አበረታች ውጤትም እየተመዘገበ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በበጋ ወራት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ ለማከናወን ዝግጅት ተደርጓል
Nov 7, 2025 22
ጎንደር፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በዘንድሮ የበጋ ወራት በ879 ነባርና አዲዲስ ተፋሰሶች ላይ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የተፈጥሮ ሀብት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል፡፡ የመምሪያው ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ እንደገለጹት፤ ባላፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና የልማት ሥራዎች የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት በማሳደግ ተጨባጭ ለውጥ አምጥተዋል፡፡ ባገገሙ ተፋሰሶች ላይ አርሶ አደሩን በንብ ማነብ፣ በእንስሳት ማድለብ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማትና በሌሎች የልማት ሥራዎች በማሳተፍ የተሻለ ገቢ እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል፡፡ በቅድመ ዝግጅት ወቅት በዞኑ በተለያዩ ወረዳዎች ከ473 ሺህ በላይ ተሳታፊ አርሶ አደሮችን በ3ሺህ 66 የልማት ቡድኖች የማደራጀት ሥራ መከናወኑንም አስረድተዋል፡፡ ከ41ሺህ ሄክታር በላይ የተራቆቱ መሬቶች ላይ የእርከንና ክትር ሥራዎችን ጨምሮ የውሃ ስርገትን የሚጨምሩ የልማት ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ የሚከናወንባቸውን ተፋሰሶች በመጪው የክረምት ወራት በስነ ህይወታዊ ዘዴ ለማጠናከርም ከ141 ሚሊዮን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች የማፍላት ሥራ ይከናወናል ብለዋል፡፡ ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወነው የችግኝ ተከላና ክብካቤ ሥራ የዞኑን የደን ሽፋን በአሁኑ ወቅት 14 ነጥብ 5 በመቶ ለማድረስ መቻሉን አስረድተዋል፡፡ የዞኑ አርሶ አደሮች በለሙ አካባቢዎች ኢኮኖሚያዊ ጥቅም በማግኘታቸው ለተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ልዩ ትኩረት እየሰጡ መጥተዋል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ክንዱ ዘውዱ ናቸው፡፡ በዞኑ የተቋቋሙ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ጽህፈት ቤቶች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥና ያገገሙ ተፋሰሶች ዘላቂነታቸው እንዲጠበቅ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። የላይ አርማጭሆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስረሳው ደሴ በበኩላቸው እንዳሉት ወረዳቸው በተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ ሞዴል ከሚባሉ ወረዳዎች የሚጠቀስ ነው። አርሶ አደሮችም በለሙ ተፋሰሶች ላይ በንብ ማነብና በፍራፍሬ ልማት በመሰማራት የተሻለ ገቢ በማግኘት ኑሮዋቸውን እየለወጡ መምጣታቸውን አስረድተዋል።
በአርሲ ዞን ከ300 ሺህ በላይ የወተት ላሞችን በሰው ሰራሽ ስነ ዘዴና በመደበኛ መንገድ የማዳቀል ስራ እየተከናወነ ነው
Nov 7, 2025 43
አዳማ ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):-በአርሲ ዞን በበጀት ዓመቱ ከ300 ሺህ በላይ የወተት ላሞችን በሰው ሰራሽ ስነ ዘዴ እና በመደበኛ የማዳቀል ስራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለፀ። የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ቃሶ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመንና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በበጀት ዓመቱም በሰው ስራሽ ስነ ዘዴና በመደበኛ መንገድ 300 ሺህ የወተት ላሞችን ዝሪያ ለማሻሻል በዘመቻ መልክ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በእስከ አሁኑ ሂደትም ከ130 ሺህ በላይ የወተት ላሞችን ማዳቀል መቻሉን ጠቅሰው እቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት እየተሰራ ነው ብለዋል። ከማዳቀል ስራው ጎን ለጎን የተሻለ የወተትና የስጋ ምርት መስጠት የሚችሉ ዝሪያቸው የተሻሻለ ጥጃዎች ለአርሶ አደሩ እየቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል። የተጀመረው እንቅስቃሴ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተው አርሶ አደሩም በእንስሳት ዝሪያ ማሻሻያ ዘዴዎች ላይ ግንዛቤ እንዲኖረው ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሚናውን ማጠናከር ይጠበቅበታል-ቢሮው
Nov 7, 2025 46
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 28/2018(ኢዜአ)፡- የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ሃሰተኛና የተዛቡ መረጃዎችን በማጋለጥ በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሚናውን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅበት የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለጸ። የተሳሳቱ መረጃዎችን በመከላከል እና እውነተኛ መረጃን በማጣራት ዙሪያ ያተኮረ ስልጠና ለሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን አመራሮች እና ባለሙያዎችን በባሕር ዳር ከተማ ተሰጥቷል። በስልጠናው መድረክ የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ደጀኔ ልመንህ እንዳመለከቱት፤ በክልሉ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ትክክለኛና ተጨባጭ መረጃ ለማሕበረሰቡ በማድረስ ለዘላቂ ሰላም ግንባታው አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ የሆነውን የፅንፈኛውን ቡድን ጥፋት ሕዝቡ እየተረዳ ተግባሩን ማጋለጥና አምርሮም እየተቃወመው መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት ችግሩን በመነጋገር በሰለጠነ አግባብ ለመፍታት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ማድረጉን አስታውሰው፤ በዚህም በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች ከተሳሳተ መንገዳቸው በመውጣት መመለሳቸውን አውስተዋል። ለተመላሾችም የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት፣ የስራ እድል በመፍጠር፣ መቋቋሚያ ገንዘብና መሰል ድጋፎችን በማድረግ ከማሕበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው ሕይወታቸውን እየቀየሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። መንግስት አሁንም ለሰላምና ንግግር በሩ ክፍት እንደሆነ አንስተው፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት አፍራሽና ሃሰተኛ መረጃዎችን በማጋለጥ ሚናውን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሙሉነህ ዘበነ በበኩላቸው፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የመንግስትን የሰላም ግንባታና የልማት አጀንዳዎች በጠራ መረጃ ላይ ተመስርቶ በቅንጅትና በትብብር ማድረስ እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የክልሉን ዘላቂ ሰላም በመገንባት ሂደት የተዛባና ጥላቻ ተኮር ወሬን በማጋለጥ የላቀ ሚናውን ሊወጣ ይገባል ያሉት ደግሞ የክልሉ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሃላፊና የመድረኩ ጹሑፍ አቅራቢ አየለ አናውጤ (ዶ/ር) ናቸው። አሁን ላይ ዘመኑ ያመጣቸውን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ግጭት ቀስቃሽ መረጃዎች በፍጥነት የመሰራጨት ሰፊ እድል መኖሩን ጠቅሰዋል። ባለሙያው ተለዋዋጭና ፈጣን ለሆነው የዘመኑን የመረጃ ስርጭት የሚመጥን የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በመገንባትም በቴክኖሎጂ ታግዞ ትክክለኛ መረጃ በመስጠት ሃሰተኛ መረጃዎችን ማጋለጥ እንዳለበት አመልክተዋል። በመድረኩ የተቋማት የሕዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ሃላፊዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎችና ሌሎችም አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
ፖለቲካ
የጋራ ትርክትን በመገንባት የሀገርን ሰላምና አንድነት ለማጽናት የድርሻችንን እንወጣለን-የኪነ ጥበብ እና የሚዲያ ባለሙያዎች
Nov 7, 2025 28
ደሴ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):-የጋራ ትርክትን በመገንባት የሀገርን ሰላምና አንድነት ለማጽናት በሚደረገው ጥረት የድርሻንን እንወጣለን ሲሉ የኪነ ጥበብ እና የሚዲያ ባለሙያዎች ተናገሩ። የደሴ ከተማ አስተዳደር "ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ከኪነ ጥበብ ፣ ከሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና ከማህበረሰብ አንቂዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሄዷል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል ጋሻው ገብሬ በሰጠው አስተያየት እንደገለጸው፣ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የጋራ ትርክት መገንባት ላይ መስራት ከሁሉም ይጠበቃል። ለዚህም የኪነ ጥበብ ሙያውን ተጠቅሞ ህብረተሰቡን የሚያስተምሩ በጋራ ትርክት ላይ ያጠነጠኑ ስራዎችን በማቅረብ ሰላምን ለማጽናት በሚደረገው ጥረት የድርሻውን እንደሚወጣ ተናግሯል። የወሎ ባህል ቡድን ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሳሙኤል በላይ በበኩሉ፣ የጋራ ትርክትን የሚያጎለብቱና ሰላምን የሚያጸኑ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ገልጿል። በዚህም በኪነ ጥበብ ስራዎች ባህሎችን በማስተዋወቅ፣ ሰላምን በመስበክ፣ የእርስ በእርስ ግንኙነቶችን በሚያጠናክሩ ስራዎች ላይ በመሳተፍ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አክሏል። የኪነ ጥበብ ባለሙያዋ እንግዳወርቅ ካሳሁን ፤ጥበብ እያዝናናችና እያዋዛች ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለመፍጠር፣ ሰላምን ለማጽናትና የልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ያላትን አቅም ተጠቅመን እንሰራለን ብላለች። የደሴ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትግስት አበበ በበኩላቸው፣ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ዘርፉ ለሀገር ሰላም፣ ልማትና አንድነት በቁርጠኝነት መስራት አለበት ብለዋል። በዚህም የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የመረዳዳት፣ የመጠያየቅና የአብሮነት ልምዶች እንዲጎለብቱ እያደረጉ ያለውን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰኢድ ካሳው በበኩላቸው፣ ለከተማዋ ዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም በየደረጃው ውይይቶች እየተካሄዱ መሆኑን ጠቁመው አበረታች ውጤትም እየተመዘገበ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሚናውን ማጠናከር ይጠበቅበታል-ቢሮው
Nov 7, 2025 46
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 28/2018(ኢዜአ)፡- የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ሃሰተኛና የተዛቡ መረጃዎችን በማጋለጥ በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሚናውን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅበት የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለጸ። የተሳሳቱ መረጃዎችን በመከላከል እና እውነተኛ መረጃን በማጣራት ዙሪያ ያተኮረ ስልጠና ለሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን አመራሮች እና ባለሙያዎችን በባሕር ዳር ከተማ ተሰጥቷል። በስልጠናው መድረክ የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ደጀኔ ልመንህ እንዳመለከቱት፤ በክልሉ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ትክክለኛና ተጨባጭ መረጃ ለማሕበረሰቡ በማድረስ ለዘላቂ ሰላም ግንባታው አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ የሆነውን የፅንፈኛውን ቡድን ጥፋት ሕዝቡ እየተረዳ ተግባሩን ማጋለጥና አምርሮም እየተቃወመው መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት ችግሩን በመነጋገር በሰለጠነ አግባብ ለመፍታት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ማድረጉን አስታውሰው፤ በዚህም በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች ከተሳሳተ መንገዳቸው በመውጣት መመለሳቸውን አውስተዋል። ለተመላሾችም የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት፣ የስራ እድል በመፍጠር፣ መቋቋሚያ ገንዘብና መሰል ድጋፎችን በማድረግ ከማሕበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው ሕይወታቸውን እየቀየሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። መንግስት አሁንም ለሰላምና ንግግር በሩ ክፍት እንደሆነ አንስተው፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት አፍራሽና ሃሰተኛ መረጃዎችን በማጋለጥ ሚናውን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሙሉነህ ዘበነ በበኩላቸው፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የመንግስትን የሰላም ግንባታና የልማት አጀንዳዎች በጠራ መረጃ ላይ ተመስርቶ በቅንጅትና በትብብር ማድረስ እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የክልሉን ዘላቂ ሰላም በመገንባት ሂደት የተዛባና ጥላቻ ተኮር ወሬን በማጋለጥ የላቀ ሚናውን ሊወጣ ይገባል ያሉት ደግሞ የክልሉ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሃላፊና የመድረኩ ጹሑፍ አቅራቢ አየለ አናውጤ (ዶ/ር) ናቸው። አሁን ላይ ዘመኑ ያመጣቸውን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ግጭት ቀስቃሽ መረጃዎች በፍጥነት የመሰራጨት ሰፊ እድል መኖሩን ጠቅሰዋል። ባለሙያው ተለዋዋጭና ፈጣን ለሆነው የዘመኑን የመረጃ ስርጭት የሚመጥን የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በመገንባትም በቴክኖሎጂ ታግዞ ትክክለኛ መረጃ በመስጠት ሃሰተኛ መረጃዎችን ማጋለጥ እንዳለበት አመልክተዋል። በመድረኩ የተቋማት የሕዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ሃላፊዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎችና ሌሎችም አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በህዳር ወር በአንጎላ ይካሄዳል
Nov 6, 2025 170
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፡- ሰባተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ህዳር 15 እና 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአንጎላ ሉዋንዳ ይደረጋል። ጉባኤውን የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾና የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት አንቶኒዮ ኮስታ በጋራ ይመሩታል። የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ የህብረቱ ሀገራት መሪዎች፣ የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን እና ሌሎች የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ወጣቶች፣ የሲቪክ ማህበራትና የንግድ ልዑካን በጉባኤው ይሳተፋሉ። የሁለቱ ተቋማት አጋርነት 25 ዓመታትን ባስቆጠረበት ወቅት የሚካሄደው ይህ ጉባኤ ኢ-ተገማችነት እያደገ በመጣበት ዓለም እና የጂኦ ፖለቲካ ምህዳሮች እየተቀየሩ ባሉበት ጊዜ የሚከናወን መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የተቋማቱ መሪዎች ለባለብዙ ወገን ትብብር፣ አጋርነት እና እየታዩ ላሉ ፈተናዎች የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እንደሚገልጹ አስታውቋል። ሰላም፣ ደህንነት፣ የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት፣ ፍልሰት እና የሰዎች እንቅስቃሴና የሰው ኃይል ልማት ውይይት ከሚደረጉባቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የሚወያዩባቸው ጉዳዮች በአጀንዳ 2063፣ በዘላቂ የልማት ግቦችና የአፍሪካ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት የ2030 የጋራ ራዕይ ጋር የተቆራኙ መሆናቸው ተመላክቷል። ከዋናው የመሪዎች ጉባኤ አስቀድሞ የወጣቶች እና የሲቪክ እንዲሁም የንግድ ፎረሞች ይካሄዳሉ። በፎረሞቹ ላይ ወጣት መሪዎች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማትና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት የሚያነሷቸው ሀሳቦች በመሪዎች ጉባኤ ላይ እንደሚቀርቡ ህብረቱ ገልጿል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እ.አ.አ በ2022 በቤልጂየም መካሄዱ የሚታወስ ነው። በወቅቱ በነበረው ጉባኤ የሁለቱ ተቋማት አባል ሀገራት የ2030 የጋራ ራዕይ ማዕቀፍ ያፀደቁ ሲሆን 150 ቢሊዮን ዩሮ ገደማ የኢንቨስትመንት ማዕቀፍ ይፋ ሆኗል። የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት አጋርነት በይፋ የተጀመረው እ.አ.አ በ2000 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ታላቅ አየር ኃይል እየተገነባ ነው -ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
Nov 6, 2025 238
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 27/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ታላቅ አየር ኃይል እየተገነባ ነው ሲሉ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ። ዋና አዛዡ ከቢሾፍቱ ከተማ እና አካባቢው ነዋሪዎች ጋር 90ኛ ዓመት የአየር ኃይል የምስረታ ቀን አከባበርን አስመልክቶ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም የኢትዮጵያ አየር ኃይል በየዘመናቱ የሀገርን ሉዓላዊነት በማስከበር ረገድ አኩሪ ገድል መፈፀሙን ዋና አዛዡ ገልፀዋል። አሁንም የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥንና የሕዝባችን መመኪያ የሆነ ተቋም እየተገነባ ነው ብለዋል። "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነት እና የአንድነት ምልክት "በሚል መሪ ሐሳብ 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚያከብርም አስታውቀዋል። የምስረታ ቀኑ በአቪዬሽን ኤክስፖ፣ በአየር ትርኢት እና በሌሎችም ዝግጅቶች እንደሚከበር ተገልጿል። የምስረታ ቀኑ ለሀገር፣ ለተቋም ብሎም ለቢሾፍቱ ከተማ እድገትና የገፅታ ግንባታ የጎላ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ ከተማውን በማስዋብና ሰላሟን በመጠበቅ ነዋሪዎች ንቁ ተሳትፏቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።
ለዘላቂ ሰላም ግንባታና ለልማት ስራዎች መጠናከር ከክልሉ መንግስት ጋር ተቀራርበን እየሰራን ነው -የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Nov 6, 2025 149
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለዘላቂ ሰላም ግንባታና ለልማት ስራዎች መጠናከር ከክልሉ መንግስት ጋር ተቀራርበው እየሰሩ መሆኑን የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራሮች በክልሉ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ሰላም እና ልማት እንዲኖር ከክልሉ መንግስት ጋር በቅርበት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ የጋራ ምክር ቤቱ አባላት ለሰላምና ጸጥታ ስጋት የሆኑ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ለክልሉ መንግስት አስፈላጊ ጥቆማ እና መረጃ በመስጠት የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ ፤ የምክር ቤቱ አባል ፓርቲዎች በየቀበሌው ያለውን ሁኔታ በመከታተል ሰላምን ለማስፈን የበኩላቸውን ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። ከሰላም ጋር በተያያዘ ለውይይት የሚቀርቡ ጉዳዮች ካሲኖሩም ሀሳቦቹን በመለየት ወደ ምክር ቤቱ በማምጣት ውይይት ተደርጎበት ለመፍትሄው በጋራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ችግሮችም ሲያጋጥሙ ለመንግስት አካላት በግልጽ በማቅረብ የሰላም እና የጸጥታ ችግሮች እየተፈቱ መሆኑን ገልጸው መንግስትም ከምክር ቤቱ የሚሰጡትን አስተያየቶች ተቀብሎ እየተገበረ መሆኑን አስረድተዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ጸሐፊ አቶ ታሪኩ ድምበሩ በበኩላቸው፤ ሰላምን በማጽናት ሂደት የፖለቲካ ተዋናዮች ድርሻ አላቸው ብለዋል። የጋራ ምክር ቤቱ በተለይም የጸጥታ ስጋት ያለባቸው አካባቢዎችን በመለየት ቅድሚያ ትኩረት የሚፈልጉ እንዲሁም መሻሻል በታየባቸው ደግሞ ሰላምን ዘላቂ ከማድረግ አንጻር ከመንግስት ጋር እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምከር ቤት 22 የፖለቲካ ፓርቲዎችን በአባልነት የያዘ ምክር ቤት መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያና ሩሲያ ግንኙነትን ወደ ላቀ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሳደግ ያለመ ምክክር ተካሄደ
Nov 5, 2025 339
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 26/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያና የሩሲያ ግንኙነቶችን ወደ ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሳደግ ያለመ ምክክር ተካሂዷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እና የፋይናንስ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ሥራ አስፈፃሚ ጽሕፈት ቤት ምክትል ሀላፊ ማክሲም ኤስ ኦሬሽኪን እና ከሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ማክሲም ሬሼትኒኮቭ ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም፥በተለያዩ ስትራቴጂካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል። በተጨማሪም በዘላቂ ልማት፣ በቀጣናዊ ደኅንነት እና በጋራ ልማት ላይ መምከራቸው ተገልጿል። ሚኒስትር ጌዲዮን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሩሲያ በተለያዩ የትብብር ዘርፎች ላደረገችው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አመሥግነዋል። በቀጣይም በግብርና፣በማኑፋክቸሪንግ፣ በአይሲቲ፣ በማዕድን ልማት፣ በብረታ ብረት፣ በኢነርጂ መሠረተ ልማት፣ በኑክሊየር እና ሌሎች ዘርፎች በትብብር መሥራት የሚቻልባቸው ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታዎች መኖራቸውን አስገንዝበዋል።
የሕዳሴ ግድብ የአካባቢውን ጂኦ ፖለቲካዊ አሰላለፍ የቀየረና የዲፕሎማሲ መስኩን ስኬታማ ስራ ያረጋገጠ ነው
Nov 5, 2025 237
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአካባቢውን ጂኦ ፖለቲካዊ አሰላለፍ የቀየረና የዲፕሎማሲ መስኩን ስኬታማ ተግባር ያረጋገጠ መሆኑን ምሁራን ገለጹ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፖለቲክስና የአፍሪካ ጥናት ማዕከል መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ታፈሰ እና የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አየለ በከሪ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ማንኛውም ሉዓላዊ ሀገር ያለውን የተፈጥሮ ሀብት አልምቶ የመጠቀም ሙሉ መብት እንዳለው አስታውቀዋል፡፡ ምሁራኑ ኢትዮጵያ ሌሎችን በማይጎዳ መልኩ በሃብቶቿ የመጠቀም መብት እንዳላት ጠቅሰው፤ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የሚደረጉ ተግባራት መጠናከር አለባቸው ብለዋል። የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አየለ በከሪ፤ ኢትዮጵያ የጀመረቻቸው ፕሮጀክቶች ብሔራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ ባለፈ ዜጎችን ከድህነት ለማውጣት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፖለቲክስና የአፍሪካ ጥናት ማዕከል መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ታፈሰ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ግንባታን በተመለከተ ይሰነዘሩባት የነበሩ ጫናዎችን ለመቋቋም ውጤታማ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ማከናወኗን አስታውሰዋል፡፡ በመንግስትና በዜጎች ትብብር የተከናወኑ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ስራዎች ፀረ ኢትዮጵያ አቋም ሲያራምዱ የነበሩ አካላትን ከኢትዮጵያ ጎን እንዲቆሙ አድርጓል ነው ያሉት። ፕሮፌሰር አየለ በከሪ ኢትዮጵያ የታላቁን የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ዓለም አቀፍ ሕግን አክብራ ማጠናቀቋንም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የተከተለችው አካሄድ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር የምታደርገውን ጥረት ማንም ሊያስቆመው እንደማይችል ያሳየ መሆኑን አመልክተው፤ ይህም ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዳይ መሆኑን ነው የጠቀሱት። ግብጽ የዓባይን ወንዝ በበላይነት የመቆጣጠር ፍላጎቷ ማብቃቱን በመገንዘቧ የቀይ ባህር መድረክ የሚል ቡድን ማቋቋሟን ተናግረዋል፡፡ ግብጽ በመድረኩ በመታገዝ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ጉዳይ ምንም ዓይነት ተሳትፎ እንዳይኖራት ጥረት እያደረገች መሆኑን አንስተዋል። ይህንኑ እንቅስቃሴ ለመመከት የተጠናከሩ የዲፕሎማሲ ስራዎች እንደሚያስፈልጉ ነው ያነሱት። ፕሮፌሰር ተስፋዬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በአካባቢው ያለውን የጂኦ ፖለቲካዊ አሰላለፍ የቀየረና በዲፕሎማሲ መስክ የተገኘውን ድል ያረጋገጠ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሞቿን ለማረጋገጥ በዲፕሎማሲው መስክ ያከናወነቻችው ተግባራት ውጤታማ እንዳደረጓት ነው የተናገሩት።
የምስራቅ ዕዝ በተሰማራባቸው ግዳጆች ሁሉ በጀግንነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሀገሩ ዳር ድንበርና የሉአላዊነቷ ዘብ ሆኖ ቆሟል
Nov 5, 2025 251
ሐረር፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ ዕዝ በተሰማራባቸው ግዳጆች ሁሉ በጀግንነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሀገሩ ዳር ድንበርና የሉአላዊነቷ ዘብ ሆኖ መቆሙ ተገልጿል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ ዕዝ፤ በምስራቅ ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ተሰማርቶ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት እየተወጣ ይገኛል። በተለይም በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አሸባሪው አልሸባብ ሾልኮ በመግባት የኢትዮጵያ የልማትና የሰላም እንከን እንዳይሆን ዕዙ አስተማማኝ መከታ ሆኖ ሌት ከቀን ግዳጁን እየተወጣ መሆኑ ይታወቃል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ ዕዝ 305ኛ ኮር ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ኮሎኔል ማርሼት ፈለገ፤ ዕዙ በተሰማራባቸው ግዳጆች ሁሉ በጀግንነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሀገሩ ዳር ድንበርና የሉአላዊነቷ ዘብ ሆኖ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የቀጠናውን ሠላም የማረጋገጥና የምስራቁን የሀገሪቷን አካባቢዎች ሰላምና ደህንነት አስተማማኝ በማድረግና ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲከናወኑ ሌት ከቀን በመቆም ተልዕኮውን በላቀ ብቃትና በቁርጠኝነት እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኮሩ አባላት በቀጣናው የሚንቀሳቀሱ ፀረ-ሰላም ሀይሎችን ተከታትለው እርምጃ በመውሰድ በአካባቢው ምንም አይነት ስጋት እንዳይኖር እየሰሩ መሆኑንም አረጋግጠዋል። በምስራቅ ኢትዮጵያ አገልግሎት የጀመሩ እና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ምንም አይነት መሰናክል እንዳይገጥማቸው ኮሩ በአስተማማኝ ጥበቃ እያደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል። የዕዙ የ28ኛ ክፍለጦር 2ኛ ሬጅመንት 1ኛ ሻምበል አዛዥ መቶ አለቃ ጌታሰው ጋሻው በበኩላቸው፤ዕዙ በተለይም በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አሸባሪው አል ሸባብ፣ ሌሎች የውጭ ጠላቶች ለኢትዮጵያ ሰላምና ልማት ስጋት እንዳይሆኑ ግዳጅና ሃላፊነቱን በላቀ ብቃት እየተወጣ መሆኑን አንስተው ይህንንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የዕዙ የ27ኛ ክፍለጦር ዘመቻ መኮንን መቶ አለቃ ጌታ መሳይ ዳዊት፤ዕዙ ለሀገሩ ዳር ድንበርና ለሉአላዊነቷ መከበር በጀግንነት፣ በላቀ ብቃትና በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የኤፒሲ ብረት ለበስ አዛዥ መቶ አለቃ ደጀኔ አበበ በበኩላቸው ዕዙ በምስራቅ ኢትዮጵያና በድንበር አካባቢዎች አስተማማኝ መከታ ሆኖ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ላይ ሊቃጣ የሚችል ትንኮሳ ካጋጠመ ፈጣንና የማያዳግም እርምጃ መውሰድ የሚችል፤ በየትኛውም ስፍራ እና የአየር ሁኔታ ግዳጁን በላቀ ብቃት የሚወጣ አስተማማኝና ጠንካራ ሰራዊት ተገንብቷል ሲሉም አረጋግጠዋል።
ፖለቲካ
የጋራ ትርክትን በመገንባት የሀገርን ሰላምና አንድነት ለማጽናት የድርሻችንን እንወጣለን-የኪነ ጥበብ እና የሚዲያ ባለሙያዎች
Nov 7, 2025 28
ደሴ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):-የጋራ ትርክትን በመገንባት የሀገርን ሰላምና አንድነት ለማጽናት በሚደረገው ጥረት የድርሻንን እንወጣለን ሲሉ የኪነ ጥበብ እና የሚዲያ ባለሙያዎች ተናገሩ። የደሴ ከተማ አስተዳደር "ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ከኪነ ጥበብ ፣ ከሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና ከማህበረሰብ አንቂዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሄዷል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል ጋሻው ገብሬ በሰጠው አስተያየት እንደገለጸው፣ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የጋራ ትርክት መገንባት ላይ መስራት ከሁሉም ይጠበቃል። ለዚህም የኪነ ጥበብ ሙያውን ተጠቅሞ ህብረተሰቡን የሚያስተምሩ በጋራ ትርክት ላይ ያጠነጠኑ ስራዎችን በማቅረብ ሰላምን ለማጽናት በሚደረገው ጥረት የድርሻውን እንደሚወጣ ተናግሯል። የወሎ ባህል ቡድን ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሳሙኤል በላይ በበኩሉ፣ የጋራ ትርክትን የሚያጎለብቱና ሰላምን የሚያጸኑ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ገልጿል። በዚህም በኪነ ጥበብ ስራዎች ባህሎችን በማስተዋወቅ፣ ሰላምን በመስበክ፣ የእርስ በእርስ ግንኙነቶችን በሚያጠናክሩ ስራዎች ላይ በመሳተፍ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አክሏል። የኪነ ጥበብ ባለሙያዋ እንግዳወርቅ ካሳሁን ፤ጥበብ እያዝናናችና እያዋዛች ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለመፍጠር፣ ሰላምን ለማጽናትና የልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ያላትን አቅም ተጠቅመን እንሰራለን ብላለች። የደሴ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትግስት አበበ በበኩላቸው፣ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ዘርፉ ለሀገር ሰላም፣ ልማትና አንድነት በቁርጠኝነት መስራት አለበት ብለዋል። በዚህም የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የመረዳዳት፣ የመጠያየቅና የአብሮነት ልምዶች እንዲጎለብቱ እያደረጉ ያለውን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰኢድ ካሳው በበኩላቸው፣ ለከተማዋ ዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም በየደረጃው ውይይቶች እየተካሄዱ መሆኑን ጠቁመው አበረታች ውጤትም እየተመዘገበ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሚናውን ማጠናከር ይጠበቅበታል-ቢሮው
Nov 7, 2025 46
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 28/2018(ኢዜአ)፡- የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ሃሰተኛና የተዛቡ መረጃዎችን በማጋለጥ በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት ሚናውን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅበት የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለጸ። የተሳሳቱ መረጃዎችን በመከላከል እና እውነተኛ መረጃን በማጣራት ዙሪያ ያተኮረ ስልጠና ለሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን አመራሮች እና ባለሙያዎችን በባሕር ዳር ከተማ ተሰጥቷል። በስልጠናው መድረክ የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ደጀኔ ልመንህ እንዳመለከቱት፤ በክልሉ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ትክክለኛና ተጨባጭ መረጃ ለማሕበረሰቡ በማድረስ ለዘላቂ ሰላም ግንባታው አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ የሆነውን የፅንፈኛውን ቡድን ጥፋት ሕዝቡ እየተረዳ ተግባሩን ማጋለጥና አምርሮም እየተቃወመው መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት ችግሩን በመነጋገር በሰለጠነ አግባብ ለመፍታት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ማድረጉን አስታውሰው፤ በዚህም በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች ከተሳሳተ መንገዳቸው በመውጣት መመለሳቸውን አውስተዋል። ለተመላሾችም የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት፣ የስራ እድል በመፍጠር፣ መቋቋሚያ ገንዘብና መሰል ድጋፎችን በማድረግ ከማሕበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው ሕይወታቸውን እየቀየሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። መንግስት አሁንም ለሰላምና ንግግር በሩ ክፍት እንደሆነ አንስተው፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት ለማፅናት አፍራሽና ሃሰተኛ መረጃዎችን በማጋለጥ ሚናውን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሙሉነህ ዘበነ በበኩላቸው፤ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የመንግስትን የሰላም ግንባታና የልማት አጀንዳዎች በጠራ መረጃ ላይ ተመስርቶ በቅንጅትና በትብብር ማድረስ እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የክልሉን ዘላቂ ሰላም በመገንባት ሂደት የተዛባና ጥላቻ ተኮር ወሬን በማጋለጥ የላቀ ሚናውን ሊወጣ ይገባል ያሉት ደግሞ የክልሉ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሃላፊና የመድረኩ ጹሑፍ አቅራቢ አየለ አናውጤ (ዶ/ር) ናቸው። አሁን ላይ ዘመኑ ያመጣቸውን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ግጭት ቀስቃሽ መረጃዎች በፍጥነት የመሰራጨት ሰፊ እድል መኖሩን ጠቅሰዋል። ባለሙያው ተለዋዋጭና ፈጣን ለሆነው የዘመኑን የመረጃ ስርጭት የሚመጥን የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በመገንባትም በቴክኖሎጂ ታግዞ ትክክለኛ መረጃ በመስጠት ሃሰተኛ መረጃዎችን ማጋለጥ እንዳለበት አመልክተዋል። በመድረኩ የተቋማት የሕዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ሃላፊዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎችና ሌሎችም አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በህዳር ወር በአንጎላ ይካሄዳል
Nov 6, 2025 170
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፡- ሰባተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ህዳር 15 እና 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአንጎላ ሉዋንዳ ይደረጋል። ጉባኤውን የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾና የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት አንቶኒዮ ኮስታ በጋራ ይመሩታል። የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ የህብረቱ ሀገራት መሪዎች፣ የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን እና ሌሎች የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ወጣቶች፣ የሲቪክ ማህበራትና የንግድ ልዑካን በጉባኤው ይሳተፋሉ። የሁለቱ ተቋማት አጋርነት 25 ዓመታትን ባስቆጠረበት ወቅት የሚካሄደው ይህ ጉባኤ ኢ-ተገማችነት እያደገ በመጣበት ዓለም እና የጂኦ ፖለቲካ ምህዳሮች እየተቀየሩ ባሉበት ጊዜ የሚከናወን መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የተቋማቱ መሪዎች ለባለብዙ ወገን ትብብር፣ አጋርነት እና እየታዩ ላሉ ፈተናዎች የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እንደሚገልጹ አስታውቋል። ሰላም፣ ደህንነት፣ የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የአየር ንብረት ለውጥ አይበገሬነት፣ ፍልሰት እና የሰዎች እንቅስቃሴና የሰው ኃይል ልማት ውይይት ከሚደረጉባቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የሚወያዩባቸው ጉዳዮች በአጀንዳ 2063፣ በዘላቂ የልማት ግቦችና የአፍሪካ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት የ2030 የጋራ ራዕይ ጋር የተቆራኙ መሆናቸው ተመላክቷል። ከዋናው የመሪዎች ጉባኤ አስቀድሞ የወጣቶች እና የሲቪክ እንዲሁም የንግድ ፎረሞች ይካሄዳሉ። በፎረሞቹ ላይ ወጣት መሪዎች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማትና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት የሚያነሷቸው ሀሳቦች በመሪዎች ጉባኤ ላይ እንደሚቀርቡ ህብረቱ ገልጿል። ስድስተኛው የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እ.አ.አ በ2022 በቤልጂየም መካሄዱ የሚታወስ ነው። በወቅቱ በነበረው ጉባኤ የሁለቱ ተቋማት አባል ሀገራት የ2030 የጋራ ራዕይ ማዕቀፍ ያፀደቁ ሲሆን 150 ቢሊዮን ዩሮ ገደማ የኢንቨስትመንት ማዕቀፍ ይፋ ሆኗል። የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት አጋርነት በይፋ የተጀመረው እ.አ.አ በ2000 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ታላቅ አየር ኃይል እየተገነባ ነው -ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
Nov 6, 2025 238
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 27/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ታላቅ አየር ኃይል እየተገነባ ነው ሲሉ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ። ዋና አዛዡ ከቢሾፍቱ ከተማ እና አካባቢው ነዋሪዎች ጋር 90ኛ ዓመት የአየር ኃይል የምስረታ ቀን አከባበርን አስመልክቶ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም የኢትዮጵያ አየር ኃይል በየዘመናቱ የሀገርን ሉዓላዊነት በማስከበር ረገድ አኩሪ ገድል መፈፀሙን ዋና አዛዡ ገልፀዋል። አሁንም የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥንና የሕዝባችን መመኪያ የሆነ ተቋም እየተገነባ ነው ብለዋል። "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነት እና የአንድነት ምልክት "በሚል መሪ ሐሳብ 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚያከብርም አስታውቀዋል። የምስረታ ቀኑ በአቪዬሽን ኤክስፖ፣ በአየር ትርኢት እና በሌሎችም ዝግጅቶች እንደሚከበር ተገልጿል። የምስረታ ቀኑ ለሀገር፣ ለተቋም ብሎም ለቢሾፍቱ ከተማ እድገትና የገፅታ ግንባታ የጎላ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ ከተማውን በማስዋብና ሰላሟን በመጠበቅ ነዋሪዎች ንቁ ተሳትፏቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።
ለዘላቂ ሰላም ግንባታና ለልማት ስራዎች መጠናከር ከክልሉ መንግስት ጋር ተቀራርበን እየሰራን ነው -የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
Nov 6, 2025 149
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለዘላቂ ሰላም ግንባታና ለልማት ስራዎች መጠናከር ከክልሉ መንግስት ጋር ተቀራርበው እየሰሩ መሆኑን የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራሮች በክልሉ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ሰላም እና ልማት እንዲኖር ከክልሉ መንግስት ጋር በቅርበት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ የጋራ ምክር ቤቱ አባላት ለሰላምና ጸጥታ ስጋት የሆኑ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ለክልሉ መንግስት አስፈላጊ ጥቆማ እና መረጃ በመስጠት የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ ፤ የምክር ቤቱ አባል ፓርቲዎች በየቀበሌው ያለውን ሁኔታ በመከታተል ሰላምን ለማስፈን የበኩላቸውን ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። ከሰላም ጋር በተያያዘ ለውይይት የሚቀርቡ ጉዳዮች ካሲኖሩም ሀሳቦቹን በመለየት ወደ ምክር ቤቱ በማምጣት ውይይት ተደርጎበት ለመፍትሄው በጋራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ችግሮችም ሲያጋጥሙ ለመንግስት አካላት በግልጽ በማቅረብ የሰላም እና የጸጥታ ችግሮች እየተፈቱ መሆኑን ገልጸው መንግስትም ከምክር ቤቱ የሚሰጡትን አስተያየቶች ተቀብሎ እየተገበረ መሆኑን አስረድተዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ጸሐፊ አቶ ታሪኩ ድምበሩ በበኩላቸው፤ ሰላምን በማጽናት ሂደት የፖለቲካ ተዋናዮች ድርሻ አላቸው ብለዋል። የጋራ ምክር ቤቱ በተለይም የጸጥታ ስጋት ያለባቸው አካባቢዎችን በመለየት ቅድሚያ ትኩረት የሚፈልጉ እንዲሁም መሻሻል በታየባቸው ደግሞ ሰላምን ዘላቂ ከማድረግ አንጻር ከመንግስት ጋር እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምከር ቤት 22 የፖለቲካ ፓርቲዎችን በአባልነት የያዘ ምክር ቤት መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያና ሩሲያ ግንኙነትን ወደ ላቀ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሳደግ ያለመ ምክክር ተካሄደ
Nov 5, 2025 339
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 26/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያና የሩሲያ ግንኙነቶችን ወደ ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሳደግ ያለመ ምክክር ተካሂዷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እና የፋይናንስ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ሥራ አስፈፃሚ ጽሕፈት ቤት ምክትል ሀላፊ ማክሲም ኤስ ኦሬሽኪን እና ከሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ማክሲም ሬሼትኒኮቭ ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም፥በተለያዩ ስትራቴጂካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል። በተጨማሪም በዘላቂ ልማት፣ በቀጣናዊ ደኅንነት እና በጋራ ልማት ላይ መምከራቸው ተገልጿል። ሚኒስትር ጌዲዮን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሩሲያ በተለያዩ የትብብር ዘርፎች ላደረገችው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አመሥግነዋል። በቀጣይም በግብርና፣በማኑፋክቸሪንግ፣ በአይሲቲ፣ በማዕድን ልማት፣ በብረታ ብረት፣ በኢነርጂ መሠረተ ልማት፣ በኑክሊየር እና ሌሎች ዘርፎች በትብብር መሥራት የሚቻልባቸው ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታዎች መኖራቸውን አስገንዝበዋል።
የሕዳሴ ግድብ የአካባቢውን ጂኦ ፖለቲካዊ አሰላለፍ የቀየረና የዲፕሎማሲ መስኩን ስኬታማ ስራ ያረጋገጠ ነው
Nov 5, 2025 237
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአካባቢውን ጂኦ ፖለቲካዊ አሰላለፍ የቀየረና የዲፕሎማሲ መስኩን ስኬታማ ተግባር ያረጋገጠ መሆኑን ምሁራን ገለጹ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፖለቲክስና የአፍሪካ ጥናት ማዕከል መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ታፈሰ እና የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አየለ በከሪ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ማንኛውም ሉዓላዊ ሀገር ያለውን የተፈጥሮ ሀብት አልምቶ የመጠቀም ሙሉ መብት እንዳለው አስታውቀዋል፡፡ ምሁራኑ ኢትዮጵያ ሌሎችን በማይጎዳ መልኩ በሃብቶቿ የመጠቀም መብት እንዳላት ጠቅሰው፤ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የሚደረጉ ተግባራት መጠናከር አለባቸው ብለዋል። የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አየለ በከሪ፤ ኢትዮጵያ የጀመረቻቸው ፕሮጀክቶች ብሔራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ ባለፈ ዜጎችን ከድህነት ለማውጣት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፖለቲክስና የአፍሪካ ጥናት ማዕከል መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ታፈሰ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ግንባታን በተመለከተ ይሰነዘሩባት የነበሩ ጫናዎችን ለመቋቋም ውጤታማ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ማከናወኗን አስታውሰዋል፡፡ በመንግስትና በዜጎች ትብብር የተከናወኑ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ስራዎች ፀረ ኢትዮጵያ አቋም ሲያራምዱ የነበሩ አካላትን ከኢትዮጵያ ጎን እንዲቆሙ አድርጓል ነው ያሉት። ፕሮፌሰር አየለ በከሪ ኢትዮጵያ የታላቁን የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ዓለም አቀፍ ሕግን አክብራ ማጠናቀቋንም ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የተከተለችው አካሄድ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር የምታደርገውን ጥረት ማንም ሊያስቆመው እንደማይችል ያሳየ መሆኑን አመልክተው፤ ይህም ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዳይ መሆኑን ነው የጠቀሱት። ግብጽ የዓባይን ወንዝ በበላይነት የመቆጣጠር ፍላጎቷ ማብቃቱን በመገንዘቧ የቀይ ባህር መድረክ የሚል ቡድን ማቋቋሟን ተናግረዋል፡፡ ግብጽ በመድረኩ በመታገዝ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ጉዳይ ምንም ዓይነት ተሳትፎ እንዳይኖራት ጥረት እያደረገች መሆኑን አንስተዋል። ይህንኑ እንቅስቃሴ ለመመከት የተጠናከሩ የዲፕሎማሲ ስራዎች እንደሚያስፈልጉ ነው ያነሱት። ፕሮፌሰር ተስፋዬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በአካባቢው ያለውን የጂኦ ፖለቲካዊ አሰላለፍ የቀየረና በዲፕሎማሲ መስክ የተገኘውን ድል ያረጋገጠ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሞቿን ለማረጋገጥ በዲፕሎማሲው መስክ ያከናወነቻችው ተግባራት ውጤታማ እንዳደረጓት ነው የተናገሩት።
የምስራቅ ዕዝ በተሰማራባቸው ግዳጆች ሁሉ በጀግንነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሀገሩ ዳር ድንበርና የሉአላዊነቷ ዘብ ሆኖ ቆሟል
Nov 5, 2025 251
ሐረር፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ ዕዝ በተሰማራባቸው ግዳጆች ሁሉ በጀግንነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሀገሩ ዳር ድንበርና የሉአላዊነቷ ዘብ ሆኖ መቆሙ ተገልጿል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ ዕዝ፤ በምስራቅ ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ተሰማርቶ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት እየተወጣ ይገኛል። በተለይም በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አሸባሪው አልሸባብ ሾልኮ በመግባት የኢትዮጵያ የልማትና የሰላም እንከን እንዳይሆን ዕዙ አስተማማኝ መከታ ሆኖ ሌት ከቀን ግዳጁን እየተወጣ መሆኑ ይታወቃል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ ዕዝ 305ኛ ኮር ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ኮሎኔል ማርሼት ፈለገ፤ ዕዙ በተሰማራባቸው ግዳጆች ሁሉ በጀግንነት በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት የሀገሩ ዳር ድንበርና የሉአላዊነቷ ዘብ ሆኖ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የቀጠናውን ሠላም የማረጋገጥና የምስራቁን የሀገሪቷን አካባቢዎች ሰላምና ደህንነት አስተማማኝ በማድረግና ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲከናወኑ ሌት ከቀን በመቆም ተልዕኮውን በላቀ ብቃትና በቁርጠኝነት እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኮሩ አባላት በቀጣናው የሚንቀሳቀሱ ፀረ-ሰላም ሀይሎችን ተከታትለው እርምጃ በመውሰድ በአካባቢው ምንም አይነት ስጋት እንዳይኖር እየሰሩ መሆኑንም አረጋግጠዋል። በምስራቅ ኢትዮጵያ አገልግሎት የጀመሩ እና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ምንም አይነት መሰናክል እንዳይገጥማቸው ኮሩ በአስተማማኝ ጥበቃ እያደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል። የዕዙ የ28ኛ ክፍለጦር 2ኛ ሬጅመንት 1ኛ ሻምበል አዛዥ መቶ አለቃ ጌታሰው ጋሻው በበኩላቸው፤ዕዙ በተለይም በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አሸባሪው አል ሸባብ፣ ሌሎች የውጭ ጠላቶች ለኢትዮጵያ ሰላምና ልማት ስጋት እንዳይሆኑ ግዳጅና ሃላፊነቱን በላቀ ብቃት እየተወጣ መሆኑን አንስተው ይህንንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የዕዙ የ27ኛ ክፍለጦር ዘመቻ መኮንን መቶ አለቃ ጌታ መሳይ ዳዊት፤ዕዙ ለሀገሩ ዳር ድንበርና ለሉአላዊነቷ መከበር በጀግንነት፣ በላቀ ብቃትና በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የኤፒሲ ብረት ለበስ አዛዥ መቶ አለቃ ደጀኔ አበበ በበኩላቸው ዕዙ በምስራቅ ኢትዮጵያና በድንበር አካባቢዎች አስተማማኝ መከታ ሆኖ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ላይ ሊቃጣ የሚችል ትንኮሳ ካጋጠመ ፈጣንና የማያዳግም እርምጃ መውሰድ የሚችል፤ በየትኛውም ስፍራ እና የአየር ሁኔታ ግዳጁን በላቀ ብቃት የሚወጣ አስተማማኝና ጠንካራ ሰራዊት ተገንብቷል ሲሉም አረጋግጠዋል።
ማህበራዊ
በሐረሪ ክልል በትምህርት ዘመኑ 40 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ መረሀ ግብር ተጠቃሚ ይሆናሉ
Nov 7, 2025 47
ሐረር፤ጥቅምት 28/2018(ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል በትምህርት ዘመኑ 40ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ መረሀ ግብር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ። የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት መንግስት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል። ከእነዚህ ተግባራት መካከል የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል፤የትምህርት ግብዓት ማሟላት፤ የተማሪዎች ምገባ፤ የመምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችና ሌሎችም ይጠቀሳሉ። የሐረሪ ክልላዊ መንግስትም በወሰዳቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት በትምህርት ዘርፉ የተሻሉ ውጤቶች በመመዝገብ ላይ መሆናቸው ተገልጿል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዘከሪያ አብዱልአዚዝ ለኢዜአ እንዳሉት፥ ክልሉ በትምህርት ቤቶች ደረጃ ማሻሻልና በግብዓት ማሟላት ረገድ አበረታች ስራዎችን እያከናወነ ነው። ከዚሁ ጎን ለጎን የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርንም በገጠር እና በከተማ በሚገኙ 67 ቅድመ መደበኛና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል። የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር የተመጣጠነ ምግብን በማቅረብ ተማሪዎች በትምህርታቸው ውጤታማ የሚሆኑበትንና ማርፈድና መጠነ ማቋረጥን በእጅጉ እየቀነሰ ነው ብለዋል። ተግባሩ የመማር ማስተማር ስራዎችን በማቀላጠፍ የተማሪዎች ውጤትን በማሻሻሉ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ለማፍራት ማገዙን ጠቁመዋል። የክልሉ መንግስት ለተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር አስፈላጊውን በጀት መመደቡን አንስተው፥በዚህም ከቅድመ መደበኛ እስከ አንደኛ ደረጃ ያሉ 40 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች የፕሮግራሙ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አብራርተዋል። ለመጋቢ እናቶች ስልጠና የመስጠት እና ሌሎች አስፈላጊ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።
የመንግሥታቱ ድርጅት የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚያስችሉ ጥረቶች እንዲጠናከሩ ጥሪ ቀረበ
Nov 7, 2025 100
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የተነደፉ ስትራቴጂዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቀረበች። በትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፥ የተመራ ልዑክ በኡዝቤኪስታን በተካሄደው 43ኛው የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ጠቅላላ ጉባዔ ላይ መሳተፉን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ዩኔስኮ ሴክሬታሪ ጄኔራል ዓለሙ ጌታሁን ለኢዜአ ተናግረዋል። ሚኒስትሩ በጉባዔው ላይ ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ዓመታት በትምህርት፣ባህል፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና ከብዝኃ-ሕይወት ዘርፍ ጋር በተያያዘ ያከናወነቻቸውን እና እየሠራቻቸው ያሉ ተግባራትን ማብራራታቸውንም ገልጸዋል። የተባበሩት መንግሥታት የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የተነደፉ ስትራቴጂዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል ነው ያሉት። ከጉባዔው ጎን ለጎንም ከተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር የሚያስችሉ ውይይቶች ማድረጋቸውንም ሴክሬታሪ ጀኔራሉ ተናግረዋል።
የአዳማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ከማስዋብ ባለፈ ለመዝናናት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Nov 7, 2025 54
አዳማ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ)፡-የአዳማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ከማስዋብ ባለፈ ለመዝናናት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ። በአዳማ ከተማ በኮሪደር ልማት ስራ አረንጓዴና የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች፣ የብስክሌትና የእግረኛ መንገድ፣ የህፃናትና ታዳጊዎች መጫወቻ፣ የመኪና ማቆሚያዎች፣ የህዝብ መፀዳጃ ቤቶችን ያካተተ ነው። ነዋሪዎቹ የኮሪደር ልማቱ ልጆችና ታዳጊዎች የሚጫወቱበትና የሚቦርቁበት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ መጪው ትውልድ የተሻለ እንዲሆን ያደርጋል ብለዋል። በአዳማ ከተማ ወንጂ ማዞሪያ አካባቢ በሚገኝ የህዝብ መዝናኛ ፓርክ ከአራት ልጆቻቸው ጋር ሲዝናኑ ያገኘናቸው ወይዘሮ መቅደላዊት ደጀኔ በሰጡት አስተያየት በከተማዋ የተከናወነው የኮሪደር ልማት አዳማን ከተጨናነቀና ንፁህ ካልሆነ ከባቢ በማላቀቅ ተስማሚና ውብ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል። በተለይ ከልጆቻቸው ጋር ለመዝናናት የመጡበት ይህ የህዝብ ፓርክ በፊት የቆሻሻ መጣያ እንደነበር አስታውሰው አሁን ገጽታው ሙሉ በሙሉ ተቀይሮ የስፖርት ማዘውተሪያና መዝናኛ ስፍራ ሆኖ ስላገኙት መደሰታቸውን ገልጸዋል። ለተሽከርካሪም ሆነ ለእግረኛ ምቾት የማይሰጡና ለአደጋ ሲያጋልጡ የነበሩ የከተማዋ ጠባብ መንገዶች ደረጃቸውን በሚመጥን መልኩ ሰፋ ብለው መሰራታቸው፣ የአረንጓዴ ፓርክ፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገድ ማካተታቸው ደግሞ በቀንም ሆነ በምሽት ከቤተሰብ ጋር የእግር ጉዞ ለማድረግ ምቹ ሁኔታን ፈጥሮልናል ብለዋል። አቶ መሀመድ አማን፤ የኮሪደር ልማት ስራው ከተማዋን ከማስዋብ ባለፈ የመዝናኛ ቦታዎችን ያካተተ በመሆኑ ታዳጊ ህፃናትን ጨምሮ ለእንቅስቃሴና መዝናኛ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። የኮሪደር ልማቱ ወደ ኋላ ቀርቶ የነበረውን የከተማውን እድገትና ደረጃ ለማስጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ገልጸዋል። የኮሪደር ስራው የታክሲና የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችን ከመለየት ባለፈ የብስክሌትና የእግረኛ መንገዱም ለነዋሪዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። ወጣት ሮዛ ነጌሶ በበኩሏ በኮሪደር ልማት ምክንያት መንገድ በመዋቡ ለንግድ ስራም ምቹ ሁኔታ የፈጠረ መሆኑን ገልጻለች። የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ንፅህናና ውበት ከማስጠበቅ ባለፈ የአረንጓዴ ቦታዎች፣ የሕዝብ መዝናኛዎችና ማረፊያዎችን በመፍጠሩ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ በማድረጉ ልማቱን ልንጠብቅና ልንንከባከበው ይገባል ብላለች። በአጠቃላይ የኮሪደር ልማቱ ከተማውን ውብ እና ለነዋሪዎቿና ለቱሪስቶች ምቹ እንዲሁም ተመራጭ የሚያደርጋት መሆኑንም አንስታለች። በአዳማ የኮሪደር ልማትን ተከትሎ ዘመናዊና አዳዲስ የመንገድ መብራቶች መተከላቸው አካባቢውን ልዩ ገፅታ በማላበስ ከተማዋን ውብና ለኑሮ ተስማሚ እያደረገ ነው ያሉት ደግሞ አቶ አሸብር ኃይለማርያም ናቸው። በተለይ እርሳቸው የእለት ስራቸውን በሚያከናውኑበት አካባቢ በኮሪደር ልማቱ በሁለቱም የመንገድ ዳርቻዎች ለእግረኛ ምቹ መንገዶች መገንባታቸው አካባቢውን ውብ ገፅታ ከማላበስ ባለፈ የስራ አካባቢያቸውን እንዲወዱና ስራቸውን በትጋት ለመስራት እንዳነሳሳቸው ተናግረዋል።
በክልሉ የጤና መድህን አገልግሎት ለማህበረሰቡ የተሻለና ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለመስጠት እያገዘ ነው
Nov 7, 2025 57
ቦንጋ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የጤና መድህን አገልግሎት ለማህበረሰቡ የተሻለና ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለመስጠት እያገዘ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ። የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች በበኩላቸው የሚያገኙት አገልግሎት ከጊዜ ወደጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግረዋል። የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢብራሒም ተማም ለኢዜአ እንደገለጹት የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር በማሳደግ የጤና አገልግሎትን ለማህበረሰቡ በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ነው። ለዚህም በ2017 ዓ.ም በክልሉ 421ሺህ 541 እማውራና አባውራዎችን የጤና መድህን አባል ተጠቃሚ በማድረግ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ሽፋንን ከ75 ነጥብ 6 በመቶ ላይ ለማድረስ መቻሉን ጠቁመዋል። በዚሁ በጀት ዓመት ከአባላቱ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰ መቻሉን ጠቁመው፣ የአባላትን ቁጥር ከማሳደግ ባለፈ በጤና ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማሻሻል በተሰራው ሥራ ውጤት እየታየ መምጣቱን ገልጸዋል። ለዚህም ቀደም ሲል ከመድሀኒት እጥረት ጋር በተያያዘ ይነሳ የነበረ ችግር እየተፈታ መምጣቱንና በአገልግሎቱ ላይ የደንበኞች የእርካታ ማነስ መሻሻሉን በማሳያነት ጠቅሰዋል። በቀጣይም ይህን አጠናክሮ በማስቀጠል አዳዲስ አባላትን ለማፍራት፣ የላቦራቶሪ አገልግሎት ጥራትን ለማሳደግና የመድሀኒት አቅርቦት ችግርን ሙሉ ለሙሉ ለመፍታት በትኩረት ይሰራል ብለዋል። እንደ አቶ ኢብራሒም ገለጻ አገልግሎቱን ለማሻሻል በመጀመሪያ ሩብ ዓመቱ ከ139 ሚሊዮን 544 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ በክልሉ ለሚገኙ ጤና ጣቢያዎችና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ተሰጥቷል። ይህም በጤና ተቋማት የሚስተዋለውን የበጀት ችግር በማቃለል በተለይ የመደሀኒት አቅርቦቱ እንዲሻሻል ጉልህ አስተዋጾ ማድረጉን ነው የገለጹት። በዋቻ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለሕክምና የመጡት የጤና መድህን አባላት በበኩላቸው የጤና እክል ሲገጥማቸው ያለችግር መታከም እንደቻሉ ተናግረዋል። በአባልነታቸው በዓመት አንዴ የከፈሉት መዋጮ የተሻለ የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። ከተጠቃሚዎች መካከል ከቤንች ሸኮ ዞን ሰሜን ቤንች ወረዳ ለተሻለ ሕክምና ባለቤታቸውን በሪፈር ይዘው እንደመጡ የገለፁት ወይዘሮ ጀሚላ ሻፊ፣ ወደሆስፒታሉ ከመጡ አራት ወር እንደሆናቸው ገልፀዋል። በሆስፒታሉ ቆይታቸው ያለተጨማሪ ወጪ ባለቤታቸውን እያሳከሙ መሆናቸውን ጠቁመው፣ በሆስፒታሉ ከመድሀኒት አቅርቦት፣ ከመስተንግዶና ከላቦራቶሪ አገልግሎት ጋር መሻሻል ታይቷል ብለዋል። በጨና ወረዳ ቦባጎታ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ብርሃኑ አበቶ በበኩላቸው የጤና መድህን አባል ከመሆናቸው በፊት የጤና እክል ሲገጥማቸው በገንዘብ እጦት ምክንያት ፈጥነው ወደ ጤና ተቋማት እንደማይሄዱ አስታውሰዋል። የጤና መድህን አባል ከሆኑ ወዲህ ሲታመሙ ፈጥነው ወደ ሕክምና ስለሚሄዱ የሳቸውና የቤተሰቦቻቸው ጤና ሁኔታ በእጅጉ መሻሻሉን ተናግረዋል። በሆስፒታሉ ከዚህ ቀደም የወባ በሽታን ጨምሮ የሚታዘዙ ሌሎች መደሀኒቶች በበቂ ሁኔታ ስለማይገኝ ለከፍተኛ ወጪ እንዳረግ ነበር ያሉት ነዋሪው፣ አሁን ይህ ችግሩ እየተፈታ መምጣቱን ገልጸዋል። ሆስፒታሉ የሚሰጠው የጤና አገልግሎት እየተሻሻለ መምጣቱን የገለጹት ደግሞ በዋቻ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጠቅላላ ሐኪም ሙሉዓለም በላይ (ዶ/ር) ናቸው። በተለይም የማህበረሰብ ሞዴል ፋርማሲ ከተከፈተ ወዲህ በመድሀኒት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ለውጥ መታየቱን ነው የተናገሩት።
ኢኮኖሚ
የጎንደር ሁለተኛው የሥልጣኔ ዘመን ተበሠረ- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Nov 7, 2025 19
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):- የጎንደር ሁለተኛው የሥልጣኔ ዘመን ተበሠረ ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ የፋሲል ግንብ ለአራት መቶ ዓመታት ያህል የሚንከባከበው አጥቶ የእርጅና እድሜው ላይ ደርሶ ሞቱን ነበር የሚጠብቀው ሲሉ አስፍረዋል። በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አመራርና ክትትል እንደ ንሥር ታድሶ ተነሣ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአዘዞ እስከ ፒያሳ ያለው የጎንደር መንገድ ግራና ቀኙ እየተስተካከለ እና እያማረ ዳግም እየተወለደ ነው ያውም ውበት፣ ጥቅምና ምቾት ጨምሮ ብለዋል። ተጀምሮ ያለማለቅና ቆሞ የመቅረት መተረቻ የሆነው መገጭ ዛሬ ታሪኩ ተቀየረ፤ ወድቆ የመነሣት፣ ደክሞ የመበርታት ምሳሌ ሆነ ሲሉም ገልጸዋል። ወንዙ ተቀለበሰ፤አንዱን ወሳኝ ምእራፍ ተሻገረ፤እነሆ የጎንደር ሁለተኛው የሥልጣኔ ዘመን በዚህ ሰሞን ተበሠረ ሲሉም ነው የገለጹት።
በአርሲ ዞን ከ300 ሺህ በላይ የወተት ላሞችን በሰው ሰራሽ ስነ ዘዴና በመደበኛ መንገድ የማዳቀል ስራ እየተከናወነ ነው
Nov 7, 2025 43
አዳማ ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):-በአርሲ ዞን በበጀት ዓመቱ ከ300 ሺህ በላይ የወተት ላሞችን በሰው ሰራሽ ስነ ዘዴ እና በመደበኛ የማዳቀል ስራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለፀ። የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ቃሶ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመንና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በበጀት ዓመቱም በሰው ስራሽ ስነ ዘዴና በመደበኛ መንገድ 300 ሺህ የወተት ላሞችን ዝሪያ ለማሻሻል በዘመቻ መልክ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በእስከ አሁኑ ሂደትም ከ130 ሺህ በላይ የወተት ላሞችን ማዳቀል መቻሉን ጠቅሰው እቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት እየተሰራ ነው ብለዋል። ከማዳቀል ስራው ጎን ለጎን የተሻለ የወተትና የስጋ ምርት መስጠት የሚችሉ ዝሪያቸው የተሻሻለ ጥጃዎች ለአርሶ አደሩ እየቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል። የተጀመረው እንቅስቃሴ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተው አርሶ አደሩም በእንስሳት ዝሪያ ማሻሻያ ዘዴዎች ላይ ግንዛቤ እንዲኖረው ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
በቴሌ ብር የሚከናወነው የግብይት መጠን ከአምስት ነጥብ ስድስት ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል
Nov 7, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):-በቴሌ ብር የሚከናወነው የግብይት መጠን ከአምስት ነጥብ ስድስት ትሪሊዮን ብር በላይ መድረሱን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ። ኢትዮ-ቴሌኮም ግንቦት 2013 ዓ.ም የቴሌ ብር አገልግሎትን በይፋ ማስጀመሩ ይታወሳል። የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና ለኢዜአ እንዳሉት፤ መንግስት የፋይናንስ አካታችነት የሀገሪቷ ስብራት መሆኑን በመለየት አገልግሎቶችን ለማዘመን በትኩረት እየሰራ ነው። ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኛን ታሳቢ ያደረጉ የዲጂታላይዜሽን ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ቴሌ ብር ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው የሚፈልጉትን አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል። የቴሌ ብር አገልግሎት የጥሬ ገንዘብ ግብይትን ወደ ዲጂታል የቀየረ መሆኑን አንስተው፤ አሁን ላይ ከ56 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች በማፍራት ከአምስት ነጥብ ስድስት ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት መከናወኑን ተናግረዋል። በኤሌክትሮኒክ የሚከናወነው ዕለታዊ የገንዘብ ዝውውር በአማካይ 11 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቀዋል። ከ800 በላይ ተቋማት አገልግሎታቸውን ከቴሌ ብር ጋር ማስተሳሰራቸውንና ከ300 ሺህ በላይ ነጋዴዎች በቴሌ ብር እየተገበያዩ መሆናቸውን ገልፀዋል። ቴሌ ብር ገንዘብ የመላክ፣ የተለያዩ ክፍያዎችን የመፈፀምና የብድር አገልግሎት እየተሰጠበት መሆኑንም ተናግረዋል። ከ14 ሚሊዮን በላይ ለሚደርሱ ደንበኞች ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ አነስተኛ ብድር ማቅረብ መቻሉንም አብራርተዋል። የባንኮችን አገልግሎት በማናበብ የገንዘብ ዝውውርን ዘመናዊ ለማድረግ የሚያስችለው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
ጎንደር ለዓለም አሸብራቂ ከተማ እንድትሆን በትጋት መስራት ይገባል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Nov 7, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):- ጎንደር ለዓለም አሸብራቂ ከተማ እንድትሆን በትጋት መስራት እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጎንደር ጉብኝት በማድረግ የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክትን የሥራ ሁኔታ ገምግመዋል። በተጨማሪም የፋሲል ግንብ ቤተ መንግስት እድሳት ስራን ተመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፋሲል ግንብ ቤተ መንግስት ለኢትዮጵያ ታላቅ ስጦታ እና የትም የማይገኝ ታሪክ ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ይህን የመሰለ ስጦታ የሰጡን አባቶቻችን የነሱን ፈለግ ተከትለን ሀገር ብናለማ ሀገር ብንሰራ ዛሬ ኢትዮጵያ ተረጂ አትሆንም ነበር ብለዋል። የታላቆችን ስራ ማድነቅ፣ ማክበር እና መመርመር መጀመር ለዛ ስራ አንድ ጡብ ወደ ማስቀመጥ እንደሚያሸጋግር አመልክተዋል። ትናንትናችን ማስታወሻችን መታወሻችን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሰው ማስታወሻውን መታወሻውን አይዘነጋም አያጠፋም ሲሉ ተናግረዋል። ኋላውን ማስታወስ የቻለ ሰው እና ማህበረሰብ ዛሬን ለመነሻነት እና ለመስሪያነት እንደሚገለገል ገልጸዋል። በጎንደር ከተማ የተጀመሩ ስራዎች እና በፋሲል ቤተ መንግስት ግቢ ውስጥ የታየው ለውጥ ልጆቻን ከኛ የተሻለ ተስፋ እንዳላቸው ማሰብ ብቻ ሳይሆን በሚጨበጥ ነገር ለማየት ችያለሁ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። የጎንደር ልጆች አባቶች ያስረከቡትን እና ዛሬ የተሰራውን ስራ የበለጠ በሚያልቅ መልኩ በመስራት የበለጠ ያማረ፣ የተዋበ እና የለማ ሀገር ለመፍጠር የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባም አመልክተዋል። የፋሲል ቤተ መንግስት መጠገን እና መታደስ ብቻ ዳግም ነው የተወለደው ሲሉም ገልጸዋል። እንደ ፋሲል ዳግም ውልደት ሁሉ ጎንደር ዳግም እንድትወለድ የሁላችንም መሻት እና ስራ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከአዘዞ ጀምሮ እስከ ፒያሳ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ጎንደር ዳግም ውልደት መቃረቡን የሚያመለክት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህን ግብ ለማሳካት የጋራ ጥረት እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። ጎንደር ዳግም ተወልዳ ለዓለም አሸብራቂ ከተማ እስክትሆን ድረስ ሁሉም በጋራና በትጋት እንዲሰራ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የድሬዳዋ መሶብ የአንድ ማእከል እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል-ተገልጋዮች
Nov 7, 2025 59
ድሬዳዋ፣ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ)፦በድሬዳዋ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገለጹ። የድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ እና የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር እና ሌሎችም አመራሮች በተገኙበት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ስራ መጀመሩ ይታወቃል። በአገልግሎቱ በመጀመሪያው ምዕራፍ አስር የተለያዩ ተቋማት 28 አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ ታግዘው እየተሰጡ ሲሆን በዚህም በርካታ ደንበኞች አገልግሎት በማግኘት ላይ ይገኛሉ። በአገልግሎት ማእከሉ የኢዜአ ሪፖርተር ተገኝቶ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች የመሶቦ አንድ ማእከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል። መሶብ ድሬ የአንድ ማዕከል ውስጥ የተገለገሉት ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በዲጂታል አሰራር በተደራጀው ማዕከል ፈጣንና ፍትሃዊ አገልግሎት ለማግኘት አስችሏቸዋል። ከተገልጋዮቹ መካከል አቶ አበበ አሰፋ እና ወይዘሮ ብርሃኔ ወልደስላሴ፤ አገልግሎቱ ገንዘብንና ጊዜን የሚቆጥብ እንዲሁም እንግልትን የሚያስቀር በመሆኑ አስደስቶናል ብለዋል። መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ከምንም በላይ ለተገልጋዮች የላቀ ትርጉም ያለው በመሆኑ በሁሉም አካባቢዎች ቢሰፋ መልካም ነው በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ሌሎች ያነጋገርናቸው ተገልጋዮች አቶ አደም አልይ እና አቶ ፈንዲሼ ታጁ፤ በተለያዩ ተቋማት በተራራቁ አካባቢዎች ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት በአንድ ስፍራ ላይ በማግኘታችን በጣም የተደሰትንበት አሰራር ነው ብለዋል። እንዲህ አይነቱ አሰራር መሰረታዊ ለውጥ የሚታይበት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል በመሆኑ ሊሰፋ ይገባል ብለዋል። የድሬዳዋ የሲቪል ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በማዕከሉ የተጨማሪ ተቋማትን አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እያደረገ መሆኑም ታውቋል።
በክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ተኪ ምርቶችና የተለያዩ ዘርፎችን የሚደግፉ ቴክኖሎጂዎች እየተመረቱ ነው
Nov 6, 2025 115
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦በክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ተኪ ምርቶችና የተለያዩ ዘርፎችን የሚደግፉ ቴክኖሎጂዎችን እያመረቱ መሆኑ የፈጠራ ባለሙያዎች ገለጹ። "ክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም" በሀገሪቱ ውስጥ የሥራ ዕድል ፈጠራን እና የሰው ኃይል ክህሎት ማጎልበትን በተመለከተ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አማካይነት የሚመራ ሀገራዊ ተነሳሽነት ነው። ይህ ፕሮግራም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠናን (TVET) ከዘመኑ የሥራ ገበያ ፍላጎት ጋር በማጣጣም ወጣቶች ለኢኮኖሚው ዕድገት አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ለማስቻል ያለመም ነው። የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ብሩክ ሰለሞን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች ሀሳባቸውን ወደ ተግባር መቀየር የሚችሉበት ምህዳር እየተፈጠረ ነው። በዚህም የግል ዘርፉና የፋይናንስ ተቋማት ተሳትፎም እየጨመረ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም በመስኩ የተሻለ አቅም እንዲፈጠር እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በፕሮግራሙ ባለፉት ሶስት ዓመታት ከተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች የፈጠራ ሀሳብ ያላቸውን ዜጎች በማሰባሰብ የሥልጠና፣ የግብዓት፣ የቴክኖሎጂ፣ የፋይናንስ ድጋፍ ከማመቻቸት ጨምሮ የገበያ ትስስር የመፍጠር ስራዎች እየተከናወነ እንደሚገኝም አብራርተዋል። በመጀመሪያው ዙር ከ400 በላይ ወጣቶች ተሳታፊ ሆነው ከ80 በላይ ቴክኖሎጂዎች መመረታቸውን ተናግረው፤ በፕሮግራሙ ሁለተኛ ዙር በተኪ ምርቶች ላይ 152 ወጣቶች 99 ቴክኖሎጂዎችን እያለሙ ነው ብለዋል። በፕሮግራሙ በተሰጠው ድጋፍ በግብርና፣ ጤና፣ ደህንነት፣ አገልግሎት የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎች መሰራታቸውንም ተናግረዋል። ለአብነትም በአፋርና ሶማሌ ክልሎች በሰፋፊ እርሻዎች ላይ የውሃና ማዳበሪያ አጠቃቀምን በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ የሚያስችል ቴክኖሎጂ መተግበሩን ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያዊያን የተመረቱ ቴክኖሎጂዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በተካሄዱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድሮች ላይም ከፍተኛ ውጤቶች መገኘታቸውንም አንስተዋል። በቴክኖሎጂና በተኪ ምርት ስራ ከተሰማሩት የፈጠራ ባለሙያዎች መካከል ሄዋን አሊ፤ በክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ባገኘችው ድጋፍ ከሌሎች ሴቶች ጋር በመደራጀት ከውጭ የሚገቡ ማሽኖችን እያመረቱ መሆኑን ገልጻለች። የእንስሳት መኖ ማቀነባበር የሚያስችሉ አምስት መሳሪያዎችን ማምረት መቻላቸውንም ተናግራለች። ማቀነባበሪያው የእንስሳት ውጤቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ ለማድረግ እገዛ እንደሚያደርግ አብራርታለች። በሮቦቲክስና አርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ላይ የተሰማራው ወጣት ሁነኛው ዘሩ በበኩሉ የግብርናና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በሮቦት በመታገዝ ማከናወን የሚያስችል ቴክኖሎጂ መስራቱን ጠቅሷል። በሮቦቲክስና አርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ላይም የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም የስራ እድሎችን ለመፍጠር ከሌሎች ወጣቶች ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑንም ገልጿል። የፕላስቲክ ምርቶችን ማምረቻ መሳሪያ እያመረተ የሚገኘው አቤኔዘር ተከስተ፤ ማሽኑ ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለቤት ውስጥ መገልገያ የሚውሉ ፕላስቲክ ምርቶች ለማምረት እንደሚያስችል ይናገራል። ይህም የፕላስቲክ ምርቶችን በመልሶ መጠቀም የስራ እድልን ለማስፋት እንደሚረዳም ገልፅዋል፡፡ በጤና ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ያደረገችው ወጣት ነቢሃ ነስሩ፤ በጤና ተቋማት ተኝቶ ታካሚዎች አስቸኳይ እርዳታ በሚፈልጉበት ወቅት የህክምና ባለሙያዎችን በቀላሉ መጥራት እንዲችሉ እገዛ የሚያደርግ ቴክኖሎጂ ሰርታ በጤና ተቋም ጥቅም ላይ እንዲውል እየሰራች መሆኑን ጠቅሳለች። ወጣቶች የሚያጋጥሙ ችግሮችን ወደ እድሎች ለመቀየር መስራት ይኖርብናል ብላለች።
ዩኒቨርሲቲው የምርምር ስራዎችን በማከናወን አርሶ አደሩን ከተሻሻሉ የግብርና አሰራሮች ጋር እያስተዋወቀ ነው
Nov 4, 2025 285
ሮቤ፤ ጥቅምት 25/2018(ኢዜአ)፡- መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎችን በማከናወን አርሶ አደሩን ከተሻሻሉ የግብርና አሰራሮች ጋር እያስተዋወቀ መሆኑን ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው ግንባር ቀደም አርሶ አደሮች፣ የግብርና ባለሙያዎችና ተመራማሪዎችን ያሳተፈ የምርምር ማዕከላት የመስክ ምልከታን ዛሬ አካሄዷል። በመስክ ምልከታው ላይ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወንድሙ እንዳሉት ፤ ተቋሙ የአርሶ አደሩን ችግር ማዕከል ያደረጉ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ ነው። የስንዴ ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻልና በዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በምርምር ለመለየት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በአርሶ አደሩ አቅራቢያ የምርምር ጣቢያዎችን በመክፈት አርሶ አደሩን ከተሻሻሉ የግብርና አሰራሮች ጋር የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት 200 ሺህ ሄክታር በሚጠጋ ማሳ ላይ በኩታ ገጠም አስተራረስ ለተደራጁ አርሶ አደሮች ዝርያን በማላመድ፣ በአረም ቁጥጥርና በሌሎች ተዛማጅ ተግባራት ዙሪያ ሰፊ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም አመልክተዋል። በተጨማሪም ለአርሶ አደሩ የምርጥ ዘር አቅርቦትና ሌሎች የግብርና ድጋፎችን ከማድረግ በተጓዳኝ በእፅዋት በሽታ ቁጥጥርና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ተግባር ተኮር ሥልጠናና ሙያዊ ድጋፍ እየሰጠ መሆኑንም አንስተዋል። አርሶ አደሩንና የዘርፉ ባለሙያዎችን ያገናኘው የመስክ ምልከታ የዚሁ ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል። ከምሥራቅ ባሌ ዞን የመጡት አርሶ አደር ዘውዴ ጉታ፤ በስንዴ ሰብል ልማት የመሳተፍ የረጅም ዓመት ልምድ ቢኖራቸውም በምርጥ ዘር አጠቃቀም ልምድ ማነስ ምክንያት በሄክታር ከ20 ኩንታል ያልበለጠ ስንዴ ሲያመርቱ መቆየታቸውን አስታውሰዋል ። ከሦስት ዓመታት ወዲህ ግን በዩኒቨርሲቲው ድጋፍ ያገኙትን የስንዴ ምርጥ ዘር መጠቀም በመጀመራቸው በአንድ ሄክታር እስከ 70 ኩንታል ስንዴ ማምረት መጀመራቸውን አስረድተዋል። ዩኒቨርሲቲው በተወሰነ መሬት ላይ እያከናወነ ከሚገኘው የስንዴ፣ የባቄላ፣ የጤፍና የሌሎች የሰብል ዝርያዎች ብዜት ብዙ ልምድ መቅሰማቸውን የገለጹት ደግሞ ከምዕራብ አርሲ ዞን የመጡት ከማል አልይ ናቸው። የባሌ ዞን ጎባ ወረዳ አርሶ አደር አሚኖ አማን በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በተለያየ ጊዜ ምርጥ ዘርና ሌሎች ድጋፎችን አድርጎልናል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው በሚያደርግልን ድጋፍም ምርትና ምርታማነታችንን እያሻሻልን እንገኛለን ሲሉም አክለዋል። በመስክ ምልከታው ላይ ከባሌ ዞን፣ ምሥራቅ ባሌና ምዕራብ አርሲ ዞን የተውጣጡ አርሶ አደሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ኢትዮ-ኮደርስ የዜጎችን ዓለም አቀፍ የዲጂታል ተወዳዳሪነት በማሳደግ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቁልፍ ሚና እየተወጣ ነው
Nov 4, 2025 218
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 25/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮ-ኮደርስ የዜጎችን ዓለም አቀፍ የዲጂታል ተወዳዳሪነት በማሳደግ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቁልፍ ሚና እየተወጣ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢትዮ-ኮደርስ ተነሳሽነት ዜጎች የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበትን ምኅዳር እየፈጠረ የሚገኝ ሀገር አቀፍ የዲጂታል ኢትዮጵያ ልማት መርሃ ግብር አካል መሆኑ ይታዎሳል። በ5-ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ ተነሳሽነት የተጀመረው መርሃ ግብርም ዜጎች መሠረታዊ ዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት የሚያዳብሩበትን የበይነ-መረብ (ኦንላይን) የስልጠና ምኅዳር ፈጥሯል። በተነሳሽነቱም በፕሮግራሚንግ፣ በዳታ ሳይንስ፣ በአንድሮይድና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የስልጠና መስኮች ዜጎች ያለምንም ክፍያ ባሉበት ቦታ በበይነ-መረብ የስልጠና እንዲከታተሉ እያደረገ ይገኛል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የተቀዳው የኢትዮ-ኮደርስ ተነሳሽነትም ዜጎች በዲጂታል ዓለም ውስጥ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ብልጽግና ማረጋገጥ የሚያስችል ውጤቶችን እያስመዘገበ ነው። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ስዩም መንገሻ፤ የዲጂታል መሠረተ ልማቶች የመንግስትን አገልግሎቶች በማሳለጥ ተጨባጭ ስኬት እያስመዘገቡ ነው ብለዋል። የ5-ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ ተነሳሽነት ስልጠናም ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የተቀዳ ቁልፍ የዜጎች ዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት ልማት መርሃ ግብር መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮ-ኮደርስ ተነሳሽነት ስልጠናም በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ትግበራ በዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ ማህበረሰብ በመገንባት በቁልፍ መሳሪያነት እያገለገለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኮደርስ ስልጠና ከጀመረበት አንስቶም በፕሮግራሚንግ፣ አንድሮይድ፣ ዳታ ሳይንስና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሰረታዊያን ላይ 2 ነጥብ 4 ሚሊየን ዜጎች ስልጠናውን እየወሰዱ ነው ብለዋል። በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና እየተከታተሉ ከሚገኙ ዜጎች ውስጥም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን የሚሆኑት ስልጠናውን አጠናቀው ሰርትፊኬት መውሰዳቸውን አስታውቀዋል። የኮደርስ ስልጠና መርሃ ግብሩም የዜጎችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት በማሳደግ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን እያሳደገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። መርሃ ግብሩም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት የበለጸገ የሰው ሃይል በማፍራት አገልግሎት አሰጣጦችን በማዘመን በር እንደከፈተም ገልጸዋል። በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት መጨረሻም የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የወሰዱ ዜጎችን 4 ሚሊየን ለማድረስ ከክልልና ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል። ኢትዮጵያዊያንም የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠናን ባሉበት ቦታ በመመዝገብ የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት አቅማቸውን በማሳደግ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።
ስፖርት
በስፖርቱ ዘርፍ ውጤታማ ለመሆን ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ነው- ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ
Nov 7, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 28/2018(ኢዜአ)፡- አትሌቲክስን ጨምሮ በሁሉም የስፖርት ዘርፎች ውጤታማ ለመሆን ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ አስታወቀ። ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ከኢዜአ ጋር ባደረገው ቆይታ፤ በተለያዩ ስፖርት ዘርፎች እየተገኘ ያለው ውጤት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱን ተናግሯል። ከዚህ ቀደም በአትሌቲክስ ዘርፍ በተለይም በሩጫ ከፍተኛ ውጤት ሲገኝ መቆየቱን ጠቅሶ፤ አሁን ግን እየቀነሰ መምጣቱ አሳሳቢ መሆኑን ጠቁሟል። በኢትዮጵያ አትሌቲክሱን ጨምሮ በተለያዩ ስፖርቶች ላይ የተግባርና የንድፈ ሀሳብ ስልጠናው አለመመጣጠን ዋነኛ ችግር መሆኑንም አንስቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት ስፖርቱ በንድፈ ሀሳብ ላይ ብቻ አተኩሮ መመራቱ ለውጤቱ መጥፋት ምክንያት መሆኑን ጠቁሟል ። የዘርፉ ባለሙያዎች በስፖርቱ ላይ የሚታየውን የአሰራር ችግር በመፈተሽ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት በትኩረት መስራት አለባቸው ሲል አሳስቧል። በዘርፉ እየጠፋ ያለውን ውጤት ለመመለስ ተግባር ተኮር ስራ ላይ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁሞ፤ በተለይ ለስፖርቱ እድገት ጠንካራ የአሰራር ስርዓት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥቷል። እንደ ሀገር ብቁ ስፖርተኞችን ለማፍራት ከታችኛው እርከን ጀምሮ ጠንካራ የስልጠና፣ የምርጫና የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት መስራት ተገቢ መሆኑን ተናግሯል። ሁሉም አካል በኃላፊነትና በትብብር ከሰራ በሁሉም ስፖርት ዓይነቶች ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ሻለቃ ኃይሌ አስረድቷል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሃዋሳ ከተማ ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ
Nov 7, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ አምስተኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአበበ በቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ስራ ይርደው እና ፀሐይነሽ ጁላ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሃዋሳ ከተማ በውድድር ዓመቱ አራተኛ ድሉን በማስመዝገብ በ12 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በአንጻሩ አራተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በሶስት ነጥብ ከ10ኛ ደረጃ ወደ 11ኛ ዝቅ ብሏል። የአምስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ዛሬ ቀጥሎ ሲውል አዲስ አበባ ከተማ ከሸገር ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት፣ ልደታ ክፍለ ከተማ ከሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከቀኑ 9 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አምስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ዛሬ ይጀመራል
Nov 7, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአምስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከነገሌ አርሲ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሊጉ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች ሶስቱን ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። በጨዋታዎቹ አምስት ግቦችንም ሲያስቆጥር አንድ ጎል አስተናግዷል። ቡድኑ በ10 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አዲስ አዳጊው አርሲ ነጌሌ በውድድር ዓመቱ ባከናወናቸው አራት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ አቻ ወጥቷል። ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ አራት ግቦች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በሁለት ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ጨዋታው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በድል ጉዞው ለመቀጠል ነጌሌ አርሲ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን ለማስመዝገብ የሚያደርጉት ነው። በሌላኛው መርሃ ግብር ወላይታ ድቻ ከመቀሌ 70 እንደርታ ከቀኑ 10 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ወላይታ ድቻ በሊጉ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል። በጨዋታዎቹ አንድ ግብ ብቻ ሲያስቆጥር ስድስት ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን 20ኛ ደረጃ ይዟል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በሊጉ እስከ አሁን ባካሄዳቸው አራት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ሶስት ጊዜ ሲሸነፍ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። አራት ግቦችን ሲያስቆጥር ስምንት ግቦችን አስተናግዷል። ቡድኑ በአንድ ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ጨዋታው ቡድኖቹ የመጀመሪያ ድላቸውን ለማስመዝገብ የሚያደርጉት ፍልሚያ ነው። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አምስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። መቻል ሊጉን በ10 ነጥብ እየመራ ይገኛል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን የሃዋሳ ከተማ ተጫዋቾቹ ጌታነህ ከበደ እና ያሬድ ብሩክ፣ የፋሲል ከነማው በረከት ግዛው እና የመቻሉ መሐመድ አበራ በተመሳሳይ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር በጋራ ይመራሉ።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ አምስተኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል
Nov 7, 2025 60
አዲስ አበባ ፤ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የአምስተኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሶስት ጨዋታዎች በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይደረጋሉ። ከረፋዱ አራት ሰዓት ድሬዳዋ ከተማ ከሃዋሳ ከተማ ይጫወታሉ። ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች አንድ ጊዜ ሲያሸንፍ ሶስት ጊዜ ተሸንፏል። ቡድኑ በሶስት ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ሃዋሳ ከተማ ከአራት ጨዋታዎች ሶስቱን ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ሽንፈትን አስተናግዷል። ሃዋሳ ከተማ በዘጠኝ ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። አዲስ አበባ ከተማ ከሸገር ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ። አዲስ አበባ ከተማ በሶስት ነጥብ 12ኛ፣ ሸገር ከተማ በስድስት ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዘዋል። የዕለቱ የመጨረሻ መርሃ ግብር ልደታ ክፍለ ከተማ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክን ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ያገናኛል። ልደታ ክፍለ ከተማ በአምስት ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን የያዘ ሲሆን ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ12 ነጥብ ሊጉን ይመራል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካሸነፈ የሊጉን መሪነት ያጠናክራል። የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ አምስተኛ ሳምንት እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን የኢትዮ ኤሌክትሪኳ ዳግማዊት ሰለሞን በስምንት ግቦች ትመራለች። የልደታ ክፍለ ከተማዎቹ ቃልኪዳን ጥላሁንና ረድኤት ዳንኤል፣ ቱሪስት ለማ፣ ቤተልሄም መንተሎ እና ትዕግስት ወርቁ ከመቻል፣ ምትኬ ብርሃኑ ከሲዳማ ቡና፣ ፊርማዬ ከበደ ከድሬዳዋ ከተማ እና የሸገር ከተማዋ ሰናይት ኡራጎ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ይከተላሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በበጋ ወራት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ ለማከናወን ዝግጅት ተደርጓል
Nov 7, 2025 22
ጎንደር፤ ጥቅምት 28/2018 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በዘንድሮ የበጋ ወራት በ879 ነባርና አዲዲስ ተፋሰሶች ላይ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የተፈጥሮ ሀብት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል፡፡ የመምሪያው ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ እንደገለጹት፤ ባላፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና የልማት ሥራዎች የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት በማሳደግ ተጨባጭ ለውጥ አምጥተዋል፡፡ ባገገሙ ተፋሰሶች ላይ አርሶ አደሩን በንብ ማነብ፣ በእንስሳት ማድለብ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማትና በሌሎች የልማት ሥራዎች በማሳተፍ የተሻለ ገቢ እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል፡፡ በቅድመ ዝግጅት ወቅት በዞኑ በተለያዩ ወረዳዎች ከ473 ሺህ በላይ ተሳታፊ አርሶ አደሮችን በ3ሺህ 66 የልማት ቡድኖች የማደራጀት ሥራ መከናወኑንም አስረድተዋል፡፡ ከ41ሺህ ሄክታር በላይ የተራቆቱ መሬቶች ላይ የእርከንና ክትር ሥራዎችን ጨምሮ የውሃ ስርገትን የሚጨምሩ የልማት ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ የሚከናወንባቸውን ተፋሰሶች በመጪው የክረምት ወራት በስነ ህይወታዊ ዘዴ ለማጠናከርም ከ141 ሚሊዮን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች የማፍላት ሥራ ይከናወናል ብለዋል፡፡ ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወነው የችግኝ ተከላና ክብካቤ ሥራ የዞኑን የደን ሽፋን በአሁኑ ወቅት 14 ነጥብ 5 በመቶ ለማድረስ መቻሉን አስረድተዋል፡፡ የዞኑ አርሶ አደሮች በለሙ አካባቢዎች ኢኮኖሚያዊ ጥቅም በማግኘታቸው ለተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ልዩ ትኩረት እየሰጡ መጥተዋል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ክንዱ ዘውዱ ናቸው፡፡ በዞኑ የተቋቋሙ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ጽህፈት ቤቶች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥና ያገገሙ ተፋሰሶች ዘላቂነታቸው እንዲጠበቅ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። የላይ አርማጭሆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስረሳው ደሴ በበኩላቸው እንዳሉት ወረዳቸው በተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ ሞዴል ከሚባሉ ወረዳዎች የሚጠቀስ ነው። አርሶ አደሮችም በለሙ ተፋሰሶች ላይ በንብ ማነብና በፍራፍሬ ልማት በመሰማራት የተሻለ ገቢ በማግኘት ኑሮዋቸውን እየለወጡ መምጣታቸውን አስረድተዋል።
የባሌ ህዝብ ከገዳ ሥርዓት በወረሰው አስተምህሮ እና ዕሴት የተፈጥሮ ሃብቶችን በመጠበቅ አብሮ መኖርን ባህሉ ያደረገ ህዝብ ነው
Nov 5, 2025 201
ሮቤ ፤ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ የባሌ ህዝብ ከገዳ ሥርዓት በወረሰው አስተምህሮ እና ዕሴት የተፈጥሮ ኃብቶችን በመጠበቅ አብሮ መኖርን ባህሉ ያደረገ ህዝብ ነው ሲሉ የአካባቢው የሃገር ሽማግሌዎች እና ምሁራን ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ካነሱዋቸው ሀሳቦች መካከል የባሌ ህዝብ ከተፈጥሮ ሀብት ጋር ያለው መስተጋብር አንዱ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፣ “የባሌ ሕዝብ አመቺ ባልሆነ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ የጋራ የተፈጥሮ ሀብቶችን ጠብቆ በማቆየቱ ሊመሰገን ይገባል” ብለው ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዞኑ ህዝብ ያቀረቡት ምስጋናና አክብሮት የተፈጥሮ ጸጋዎችን በመንከባከብ ይበልጥ አልምቶ ለመጠቀም የሚያነሳሳ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የሃገር ሽማግሌዎች እና ምሁራን ገልጸዋል፡፡ ከሮቤ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች መካከል አቶ ተማም ጀማል፣ በተፈጥሮ ጸጋዎች የታደለው የባሌ ዞን የበርካታ ብዝሀ ህይወት ባለቤት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የቱሪዝም መዳረሻ የሆነው የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ የሐረና ጥብቅ ደንና ሌሎች ውብና ማራኪ መልካም ገጽታን የተላበሰ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ እንዳለው ጠቅሰው ፓርኩ የተለያዩ ብርቅዬ የዱር እንስሳትና አዕዋፋት መገኛ እንደሆነም አንስተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፓርኩ ልማትና ብዝሀ ህይወት ጥበቃ የሰጡት ትኩረት ብሎም ለዞኑ ህዝብ ያቀረቡት ክብርና ምስጋና በታሪክ የሚታወስና ለዘላቂ ጥበቃ የሚያነሳሳ ነው ብለዋል፡፡ በተለይ ለዘመናት ሳይለማ የተረሳው የሶፍ ኡመር ዋሻ የኢትዮጵያን ታላቅነትና መልካም ገጽታ ለአለም ህዝብ ጭምር የሚያስተዋውቅ ሌላ ቅርስ መሆኑን የገለጹት ደግሞ አቶ አማን ሐጂ አብዶ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለዞኑ ህዝብ ያቀረቡት ምስጋናና አክብሮት የተፈጥሮ ጸጋዎችንና የደን ቅሪቶችን ይበልጥ በመንከባከብ አልምቶ ለመጠቀም የሚያነሳሳ እንደሆነም አመልክተዋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢ ሳይንስ ዘርፍ መምህራንም የአገር ሽማግሌዎችን ሀሳብ በመጋራት የጋራ የተፈጥሮ ሀብቶችን በመንከባከብ ለዛሬ ላቆየው የባሌ ህዝብ በመንግስት የቀረበው እውቅናና ክብር ለዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ አዎንታዊ አንድምታ እንደሚኖረው ገልጸዋል። በተለይም በጥብቅ ደኖች አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች በአሳታፊ የደን ልማት አስተዳደር በመደራጀት ደኑን በመጠበቅ ከስነ-ምህዳሩ ከሚያገኙት ጥቅም በተጓዳኝ ከካርቦን ሽያጭ ተጨማሪ ገቢ እያገኙ መምጣታቸው የጥበቃውን ተግባር ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑንም ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲው የአካባቢ ሳይንስ ዘርፍ መምህርና ተመራማሪ ኡመር አብደላ፣ የባሌ ህዝብ ከገዳ ሥርዓት በወረሰው አስተምህሮትና ዕሴት የተፈጥሮ ኃብቶችን በመጠበቅ አብሮ መኖርን ባህሉ ያደረገ ህዝብ መሆኑን ተናግረዋል ። በተለይ የአካባቢው የተፈጥሮ ሀብት በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) በቋሚ ቅርስነት መመዝገቡን ገልፀው የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክና በውስጡ የሚገኙ የብዝሀ ህይወት ስብጥሮች ማህበረሰቡ ጠብቆ ያቆየው ሃብት መሆኑን አመልክተዋል። የባሌ ህዝብ የተፈጥሮ ኃብቱን በመንከባከብ ለትውልድ በማቆየቱ ከመንግሥት የተሰጠው እውቅና የጥበቃውን ሥራ ይበልጥ ውጤታማና ዘላቂ የሚያደርግ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላው የዘርፉ መምህርና ተመራማሪ አብዱልፈታህ አብዱ ናቸው። የተሰጠው እውቅናም የህዝቡ ብቻ ሳይሆን በዘርፉ ይስተዋሉ በነበሩ ተግዳሮቶች ዙሪያ ጥናት በማካሄድ ምክረ ሀሳብ ሲለግሱ ለቆዩት የዘርፉ ምሁራንን ጭምር የሚያነሳሳ መሆኑን አስታውሰዋል።
የአፍሪካ ሀገራት የብዝሃ ህይወት ጥበቃን የልማት አጀንዳቸው የትኩረት ማዕከል ሊያደርጉ ይገባል- ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ
Nov 4, 2025 238
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 25/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የብዝሃ ህይወት ጥበቃና እንክብካቤን እንደ ልማት አጀንዳ በመያዝ መስራት እንደሚገባቸው የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ። የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል። ጉባኤው ላለፉት ሁለት ቀናት በባለሙያዎች ደረጃ ሲከናወን ቆይቶ ዛሬ በሚኒስትሮች ደረጃ ተካሂዷል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” በመሪ መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ያለው ጉባኤ በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች የሚመክር ነው። የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር የአፍሪካ የተፈጥሮ ሀብት ከጸጋ ባሻገር የአህጉሪቱ የኢኮኖሚ እድገት፣ የምግብ ዋስትና እና የባህል ማንነት መሰረት መሆኑን አመልክተዋል። ብዝሃ ህይወት እና ተፈጥሯዊ ቅርሶች የዓለም ተፈጥሮ ሀብት ዘቦች ሆነው እያገለገሉ እንደሚገኙም ተናግረዋል። ይሁንና የአየር ንብረት ለውጥ፣ የእንስሳትና እጽዋት መኖሪያ ቦታ መውደም እና የተለያዩ ዝርያዎች መጥፋት የብዝሃ ህይወት ሀብቶች አደጋ ላይ እንዲወድቁ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። አፍሪካውያን ብዝሃ ህይወትን የአህጉሪቱ የልማት አጀንዳ ምሰሶ መሆኑን በመገንዘብ አስፈላጊውን ጥበቃ በማድረግ ቁርጠኝነታቸውን ሊያሳዩ ይገባል ነው ያሉት። በአጀንዳ 2063 የበለጸገች እና ሰላማዊ አፍሪካን የመፍጠር ህልም ሊሳካ የሚችለው በዜጎች ትጋትና በዘላቂ አካባቢ ጥበቃና አስተዳደር መሆኑንም አመልክተዋል። አህጉራዊ አጀንዳዎችን ለማሳካት የፖሊሲ ማዕቀፎችን ማጠናከር፣ በተፈጥሮ መፍትሄዎች ላይ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ እንዲሁም ወጣቶችና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን በብዝሃ ህይወት ጥበቃ የመሪነት ሚና እንዲወጡ ማድረግ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። የአፍሪካ ሀገራት ንግግራቸውን ወደ ተጨባጭ ስራ እና ወደሚለካ ውጤት በመቀየርና የአካባቢ ስነ ምህዳርን በመጠበቅ መጻኢውን ጊዜ የተሻለ ለማድረግ እንዲሰሩ አስገንዝበዋል። አፍሪካን በዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ እና ዘላቂ አጠቃቀም መሪ እናድርጋት፣ ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ነገር እናስረክብ ሲሉም ኮሚሽነሩ ጥሪ አቅርበዋል። በጉባኤው ላይ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ ነገ በመሪዎች ደረጃ በሚደረግ ስብሰባ ይጠናቀቃል። ጉባኤው ለአፍሪካ ብዝሃ ህይወት መመናመን፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ብክለት የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ መስጠት የሚያስችል መድረክ መሆኑን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኢትዮጵያ የስነ-ምህዳር እና ብዝኃ-ሕይወት ጥበቃ ስራዎች ለሌሎች ሀገራት ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው
Nov 4, 2025 217
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 25/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በስነ-ምህዳር እና ብዝኃ-ሕይወት ጥበቃ የምታከናውናቸው ተግባራት ከቀጣናው ባሻገር ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ምሳሌ መሆናቸውን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም የስነ-ምህዳርና ባዮ-ዳይቨርሲቲ ዋና የቴክኒክ አማካሪ ዶለይ ጸሪንግ ገለጹ፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም የስነ-ምህዳርና ባዮ-ዳይቨርሲቲ ዋና የቴክኒክ አማካሪ ዶለይ ጸሪንግ ኢትዮጵያ በልዩ ልዩ ስነ-ምህዳርና ብዝሃ ህይወት የታደለች ሀገር ናት ብለዋል፡፡ የብዝሃ ህይወት እና ስነ-ምህዳር ጥበቃ ለዘላቂ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ልማት ወሳኝ ሚና እንደሚያበረክት ጠቁመው፤ ተቋማቸው በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከበርካታ የዓለም ሀገራት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በብሔራዊ ፓርኮች ጥበቃን በማጠናከር እና አዳዲስ ስፍራዎችን በማልማት ለብዙ አይነት የዱር እንስሳትና ዕፅዋት ወሳኝ መኖሪያ እያለማች መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በትላልቅ የደን ልማት እያከናወነች ያለው ተግባር ከአፍሪካ ቀንድ አልፎ በዓለም አቀፉ ደረጃ ግንባር ቀደም እንደሚያደርጋት ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ በስነ-ምህዳር እና ብዝሃ ህይወት ጥበቃ ዘርፍ እያከናወነች ያለው ተግባር አስደናቂ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ስራዎች ቀጣዩን ትውልድ ጭምር ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይ ደግሞ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና ከብዝኃ-ሕይወት ጥበቃ ጋር ለማስተሳሰር እየወሰደቻቸው ያሉ እርምጃዎች የሚደነቁ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ ኢትዮጵያ በስነ-ምህዳር እና ብዝኃ-ሕይወት ጥበቃ ረገድ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ከቀጣናው ባሻገር ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ኢትዮጵያ የምታከናውነውን የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራን እንደሚያግዝም አረጋግጠዋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም በቀጣናው የሚገኙትን ሥነ-ምህዳሮችና የብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ ከመንግሥት፣ ከሲቪል ማኅበራት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ ተመራማሪ (ዶ/ር) ፋኑዔል ከበደ በበኩላቸው፤ የዱር እንስሳት ለቱሪዝም መስህብነትና ለሌሎችም ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ የእነዚህን እንስሳት መኖሪያ የመጠበቅ ስራን በትኩረት እየሰራች መሆኑን ጠቁመው በዚህም አበረታች ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡ በዚህም በርካታ የዱር እንስሳት አሁን ላይ ወደ ነባር ቀዬያቸው እየተመለሱ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 141
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 380
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል። ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
Oct 31, 2025 302
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው
Oct 24, 2025 573
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡ ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡ በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ሐተታዎች
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 65
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 358
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
የብዙዎች ቤት…
Oct 27, 2025 498
እስካሁን በተደረገ የጥናት ውጤት መሠረት ከ81 በላይ የአጥቢ እንስሣት፣ ከ450 በላይ የአዕዋፍ እና ከ400 በላይ የእፅዋት ዝርያዎች መኖሪያ ነው። ከእነዚህ መካከል አምስቱ የአዕዋፍ ዝርያዎች በዚህ ሥፍራ ብቻ ይገኛሉ፤ ከአምስቱ መካከል በተለይም የአንዷ ዝርያ ዓለም አቀፍ የዘርፉ ተመራማሪዎችንና ጎብኚዎች ቀልብ መሳቡ ይጠቀሳል። ከአካባቢው ተፈጥሯዊ አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ጋር መጣጣም የቻሉ የቆላ እፅዋት (ዛፎች) በምቾት በስፋት እንደሚገኙበትም ይገለጻል። የተመሠረተው በ1958 ዓ.ም ሲሆን፤ ስፉቱም 591 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ነው፤ በቁጥርም ሆነ በሥብጥር የብዙዎች መኖሪያ የሆነው ይህ ሥፍራ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ይሰኛል። መንግሥት በሰጠው ትኩረት ከነበረው በተሻለ ሁኔታ እንስሣቱም ሆኑ እፅዋቱ እየኖሩ ነው፤ ከሕገ ወጥ ድርጊትም እንዲጠበቁ ማድረግ መቻሉን የፓርኩ ኃላፊ አደም መሐመድ ለኢዜአ አረጋግጠዋል። በፓርኩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁንም ለ247 ወገኖች ቋሚ እና ለ2 ሺህ 535 ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ባሳለፍነው ዓመትም በ1 ሺህ 751 የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች እንደተጎበኘ ኃላፊው ገልጸዋል።
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 874
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል። ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው። የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው። ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል። ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 1808
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2164
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3030
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3128
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 1089
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 745
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6584
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5057
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ባሕር በር -የታሪክና የእድገት ስብራት ወጌሻ
Nov 5, 2025 272
ባሕር በር የታሪክ እና የእድገት ስብራት ወጌሻ በቀደሰ ተክሌ የምሥራቅ አፍሪካዋ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ስሟ ገኖ እንዲነሳ ካደረጓት መካከል የሰው ዘር መገኛነት፣ የራሷ የሆነ የአስተዳደር ሥርዓት፣ የዘመን አቆጣጠር፣ ቋንቋና ፊደል ያላት ሉዓላዊት ሀገር መሆኗ ተጠቃሽ ነው ። የገናና የጥበብ ባለቤት መሆኗን አክሱም እና ላሊበላ ዛሬም ቆመው ይመሰክሩላታል። በጥንት ጊዜ ወደብ የስልጣኔ ተጽዕኖ ፈጣሪነት መገለጫ በነበረበት ጊዜ ኢትዮጵያም ስሟ ጎልቶ ይነሳ ነበር። ወደብ ዓለምን እርስ በእርስ ከማስተሳሰር ባለፈ የግብይት የጀርባ አጥንት ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል፤ ዛሬም እያገለገለ ይገኛል። ሀገራት አዋጭ የንግድ ስትራቴጂ ቀይሰው የተለያዩ ወደቦችን የመጠቀም ልምዳቸው በታሪክ ውስጥ ጎልቶ የሚነሳ ነው። የንግድ ሥርዓታቸውን በወደብና በየብስ ከሚያከናውኑ የዓለም ሀገራት መካከል ደግሞ ኢትዮጵያ አንዷ ናት። የታሪክ ድርሳናት እንደሚያሳዩት ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘመነ መንግስታት የተለያዩ ወደቦችን በባለቤትነት አስተዳድራለች። ከአክሱም ዘመነ መንግሥት ጀምሮ እስከ ደርግ መንግስት ድረስ አዱሊስ፣ አሰብ፣ ዘይላ፣ ምጽዋና ሌሎች ወደቦችን ለኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ትገለገል ነበር። ይሕ የኢትዮጵያ የወደብ ባለቤትነት ታሪክ እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ የዘለቀ እንደነበር በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሰቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምሕርት ክፍል መምሕር አጥናፉ ምትኩ ይናገራሉ። ወደብ ከኢኮኖሚያዊ ጥቅም ባሻገር ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ፋይዳው ከፍተኛ እንደሆነም አውስተዋል። በታሪክ ኩነት ውስጥ የተፈጠረ ሴራና ተንኮል ኢትዮጵያ የባሕር በር አልባ ሀገር እንድትሆን አድርጓታል። ይሕም ከሆነ ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ ተቆጥሯል። በዚሕም ኢትዮጵያ ለወደብ ኪራይ በየዓመቱ ብዙ ቢሊዮን ብር እየከፈለች የወጪ እና ገቢ ንግድን የማንቀሳቀስ እዳ ተጭኖባታል። ይሕም የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ወደ ኋላ ከሚጎትቱ ጉዳዮች አንዱ ሆኖ ዛሬ ድረስ ዘልቋል። የወደብ አገልግሎት ነጻነት ማጣት፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ዋጋ መጨመር፣ ማዳበሪያን ጨምሮ አስፈላጊ ግብአቶች መዘግየትና በወቅቱ አለመድረስ፣ በዚሕም የሰብል ልማት ስራዎች ላይ ችግሮች መስተዋል ከባሕር በር ባለቤትነት እጦት ጋር የመያያዝ እድላቸው ሰፊ ነው። እነዚሕ ችግሮች ደግሞ ተደማምረው ለኑሮ ውድነት መፈጠር አስተዋጾኦ ይኖራቸዋል ማለት ይቻላል። በታሪክ አጋጣሚ የተፈጠረው ስብራት እያስከተለ ያለው ጉዳት አሁን ላይ ለኢትዮጵያ የሕልውና ጉዳይ በመሆኑ በታሪካዊ ዳራ መሠረት መጠገን ያስፈልጋል። ለኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ከ130 ሚሊዮን ያሻቀበ የሕዝብ ቁጥር፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና ሀገራዊ የቆዳ ስፋት ገፊ ምክንያቶች ከሚባሉት ውስጥ ይጠቀሳሉ። በሌላ በኩል ከዚሕ ቀደም የነበረው የሀገሪቱ ባሕር በር ባለቤትነት ማስረጃ ዛሬ ላይ አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። መንግሥት የጀመረው የባሕር በር ባለቤት የመሆን ጥያቄ በመሬት ተዘግቶ የመኖር ታሪክ እንዲያበቃ የሚያደርግና በዓለም አቀፍ ሕግ ተፈጥሮን በጋራ ተጠቅሞ የመልማት መብትን የሚያስጠብቅ መሆኑ እውን ነው። ለሦስት አስርት ዓመታት ታፍኖ የቆየው የቀይ ባሕር ባለቤትነት ጥያቄ የመንግስት ቁርጠኝነት እንዳለ ሆኖ ዜጎችም አጥብቀው በመያዝ መልስ እስኪያገኝ ድረስ መስራት ይጠበቃል። የሀገርና የሕዝብ የዘመናት ጥያቄ የሆነው የባሕር በር እስኪሳካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት ከሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደሚጠበቅ መምሕር አጥናፉ ይገልጻሉ። ለኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት መሆን የታሪኳና ዕድገቷ ወጌሻ ነው ያሉት መምሕር አጥናፉ ኢትዮጵያ የባሕር በር ለመጠቀም የሚያስችላት ታሪካዊ መብት አላት። ይሕን ታሪካዊ መብቷን የምታረጋግጥበት ትልቁ መሣሪያ ደግሞ ያላት ጠንካራ የዲፕሎማቲክ አቅሟ ነው። ከዓለም ሀገራት ጋር ያላት መልካም ግንኙነት ተናግሮ ለማሳመን እውነታን ለመግለጽ የሚያስችላት ነው። ይሕንንም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በዓለም ፊት አረጋግጣለች። ይሕን የሕዳሴ ድል በቀይ ባሕር ላይ የማትደግምበት ምንም ምክንያት አይኖርም። በተለይ ኢትዮጵያ ያላት የጋራ ተጠቃሚነት መርሕ በዓለም ላይ ተቀባይነት ያለውን ሀሳብ ይዛ እንድትቀርብ እያስቻላት ይገኛል። ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የሚሰጠው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲዋ ተፈጥሮን ተባብሮ በማልማት እንጠቀም የሚል መሠረት ያለው ነው። መምሕር ይስሐቅ ንጉሤ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሰቲ የምጣኔ ሀብት መምሕር ሲሆኑ የባሕር በር ጉዳይ የኢኮኖሚ ዕድገት ማጠንጠኛ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ የባሕር በር ማጣቷ በፈጣን ዕድገቷ ላይ መሰናክል ሆኖ መዝለቁን ተናግረዋል። በተለይ የዓለም ሀገራት ከፍተኛው የንግድ፣ የኢኮኖሚና ሀብት እንቅስቃሴ የሚታይበት እና የሀገራት የንግድ ልውውጥ የሚካሄድበት የቀይ ባሕር ቀጠና ላይ ያለውን አብሮ የመስራትና ከማደግ ዕድል ኢትዮጵያ ያለአግባብ መገለሏን ያነሳሉ።ይሕም በሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገትና በሌሎች ላይ ያሳደረው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ እንደሆነ ነው ያገለጹት። የባሕር በር ጥያቄ የምጣኔ ሀብት ዕድገትን በማሳለጥ ሀገሪቱ ከልመና ለመውጣት ያላትን ዕድል እንድትወስን ያስችላታል የሚሉት መምሕሩ ፤ለስኬቱም የተጀመረውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማጠናከር እንደሚገባም ነው የገለጹት። እንደ መምሕሩ ገለጻ ከዓለም አቀፍ መርሆችና ስምምነቶች እንዲሁም ካለን መልከአ ምድራዊ አቀማመጥና ታሪክ አንጻር ለኢትዮጵያ የባሕር በር ተገቢ ነው። ይሕ እንዲሳካም መንግስት ካሳየው ቁርጠኝነት በተጨማሪ ሁሉም በተቀናጀ መንገድ የሚያደርገውን ጥረት ማጠናከር ይኖርበታል። መንግስት የዘመናት የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ የቆየውን የባሕር በር ጉዳይ በግልጽና በይፋ መረጃ በመስጠት ዓለም አቀፍ አጀንዳ እንዲሆንም ጭምር እያደረገ ያለውን ጥረትንም አድንቀዋል። ታሪክ በኩነቶች መካከል መጥፎም መልካም ሆኖ ያልፋል። በታሪክ የባሕር በር ባለቤትነታችን የገጠመውን ስብራት ለመጠገን የሚያስችል ወጌሻ ያስፈልጋል። በታሪክ ሂደት መልካሙ ወደ መጥፎ ሁኔታ እንደሚቀየር ሁሉ የተበላሸን ወደ መልካም የመቀየር ዕጣ ፈንታ ያለው የዛሬው ትውልድ ላይ ነው። ለእዚሕ ደግሞ ትውልዱ በሕዳሴው ግድብ ከመንግስት ጎን ሆኖ ያሳየውን አንድነትና ሕብረት በባሕር በርም መድገም አለበት። ታሪካዊ ዳራን፣ ዲፕሎማሲን፣ ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታና ሕግን ተከትሎ በአብሮነት ከተሰራ ያኔ የተበላሸው ይቃናል፤ ያጣነውን እናገኛለን። "እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል" ዓይነት እንስሳዊ ግብር በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሊሰማ አይገባም፤ መሰማትም አይኖርበትም። ኢትዮጵያ ብታደግ ለቀጣናው ኩራት፤ ለአፍሪካም ልዕልና እንጂ ጥፋት የሚያስከትል እንዳልሆነ መገንዘብና የትብብር ልማትና ዕድገትን ባሕል ማድረግ ሊለመድ ይገባል። ሰላም!
የዳሰነቾች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ''
Oct 30, 2025 896
የዳሰነች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ'' (በጣፋጩ ሰለሞን ከጂንካ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ዳሰነቾች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በአብሮነት ተጎዳኝተው ይኖራሉ። የብሔረሰቡ አባላት ዋነኛ መተዳደሪያ ከብት እርባታ ሲሆን፤ ከከብት እርባታው ጐን ለጐን በዝቅተኛ ደረጃ በግብርናና በዓሳ ማስገር ስራ ይተዳደራሉ፡፡ ዳሰነቾች በሰሜን ከሐመር፣ በደቡብ ከኬኒያ፣ በምስራቅ ከቦረና በስተ ምዕራብ ደግሞ ከኛንጋቶም ማህበረሰብ ተጎራብተው ይኖራሉ። ዳሰነቾች ከኩሽቲክ የቋንቋ ነገድ የሚመዘዝ ''አፍ ዳሰነች'' የተሰኘ የመግባቢያ ቋንቋም አላቸው። ዳሰነቾች የተለየ የአለባበስ፣ የአጋጌጥ፣ የቤት አሰራር እና የባህላዊ የሙዚቃ ስልተ ምትን ጨምሮ አስደማሚ ባህሎች እና ማራኪ የመልክዓ ምድር አቀማመጥን የታደሉ ናቸው። ዳሰነቾች ከሚታወቁባቸው አስደማሚ ባህሎች ውስጥ አንዱ የሆነው አለመግባባቶችን በውይይት የሚፈቱበት የ''ጀለባ''ስርዓት ተጠቃሽ ነው። ይህ ስርዓት ግጭቱ ቂምና ቁርሾ በማይሻገርበት መልኩ በዘላቂነት የማስወገድ አቅም ያለው ሲሆን የማይናወጥ ሰላምና ወንድማዊ ትስስር እንዲጠናከርም ሚናው የጎላ ነው። ዕሴቱ የዳሰነቾች የአኗኗር ቁመና የሚለካበትና የሚመዘንበት መጻኢንም የሚተለምበትም ጭምር ነው። ስለሆነም በዳሰነቾች ዘንድ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል ነው የሚባለው። የባህሉ ተመራማሪ ሊዮን አርሎት 'ጀለባ'' የተሰኘው ባህላዊ ዳኝነት ከአካባቢው ሰላም አልፎ ለቀጠናው ወንድማማችነት መጠናከር ትልቅ ሚና ያለው የፍትህ ስርዓት መሆኑን ያነሳሉ። በ''በጀለባ'' ስርዓት ባህላዊ የዳኝነት አሰጣጥ እርከኖች እንዳሉ ጠቅሰው፥ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ ''ኖሞ'' የተሰኙ ሽማግሌዎች ወደ ስፍራው በማቅናት የግጭቱን መንስኤ በማጣራት ''ቶሎል'' ለተሰኙ ሌሎች ሽማግሌዎች የሚያሳውቁበት አሰራርም አላቸው። እንደ ግጭቱ ቅለትና ክብደት ''ቶሎል'' በተሰኙ ሽማግሌዎች ተለይቶ ቀለል ያለው ''ካባና'' በተሰኙ ዳኞች ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን፥ ጉዳዩ ከበድ ያለ ከሆነ ደግሞ የመጨረሻው ውሳኔ ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች ይሰጣል። ከነፍስ ማጥፋት በስተቀር ሁሉም ውሳኔዎች ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች እልባት ያገኛሉ። የነፍስ ማጥፋት ወንጀል ሲከሰት ግን ጉዳዩን ለመንግሥት አሳልፎ በመስጠት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያገኝ ይደረጋል ። ነፍስ ያጠፋው ሰው የእርምት ጊዜውን አጠናቆ ማህበረሰቡን ለመቀላቀል ሲወስን ባህላዊ የዕርቅ ስነ-ስርዓት ተዘጋጅቶ በዳይና ተበዳይ ይቅር የሚባባሉበትም ስርዓት እንዳለ የባህሉ ተመራማሪ ይናገራሉ። በዳሰነቾች ባህል ልዩነቶች ሰላማዊ በሆነ መንገድ በዘላቂነት መንገድ የመፍታት ዘመናትን የተሻገረ ድንቅ ዕሴት መኖሩን የሚያነሱት የብሔረሰቡ አባል አሸቴ ነካሲያ፤ “በዳሰነች ብሔረሰብ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል'' ይላሉ። በዳሰነቾች አለመግባባቶች በውይይት የሚፈቱበት ስርዓት እንዳለ ጠቅሰው፥ ''ናብ'' በተሰኘው የዳኝነት ስፍራ አለመግባባቶች ውለው ሳያድሩ እልባት ያገኛሉ ብለዋል። ሌላው የብሔረሰቡ አባል ሎቶያቡስ ሎኪሰሬሬ በበኩላቸው የባህል መሪዎች የተጣላን ማስታረቅ፣ ትውልዱን የመግራትና በስነ-ምግባር የማነፅ ኃላፊነት እንዳላቸው ጠቅሰዋል። ''ማንም ሰው ከባህል መሪዎች ትዕዛዝ አያፈነግጥም'' የሚሉት አቶ ሎቶያቡስ፥ ሁሉም እርስ በእርስ በመከባበር እና ችግሮች ሲኖሩ በውይይት በመፍታት አብሮነቱን ያጠናክራል ብለዋል። ወጣቱ ለባህል መሪዎች ታዛዥ ነው የሚሉት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ የብሔረሰቡ አባል ሎሲያ ሎብቻ ወጣቶች ለአካባቢው ሰላም ዘብ እንዲቆሙ፣ ከአጎራባች ህዝቦች ጋር በፍቅር እንዲኖሩ በማስተማር ወጣቱን በስነ-ምግባር የማነፅ ስራ እንደሚሰሩም ተናግረዋል። የዳሰነች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ በበኩላቸው የዳሰነች ህዝብ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ከወረዳው አልፎ ለቀጠናው ሰላም ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። የብሔረሰቡ ባህላዊ የሽምግልና ስርዓት ትውልዱን በመግራት በስነ- ምግባር የታነፀ ዜጋ እንዲፈጠር እንዳደረገም አስረድተዋል። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የሶሻል አንትሮፖሎጂ መምህርና ተመራማሪ አጎናፍር ሰለሞን፤ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓቶች ለዘመናዊው የፍትህ ስርዓት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል ብለዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች ቅጣት በመጣል ጥፋተኝነት እንዲሰማ የሚያደርጉ ሳይሆኑ፤ እውነተኛ ይቅርታን የሚያሰፍኑና ለአብሮነት የሚበጁ ዕንቁ ባህሎች እንደሆኑም አብራርተዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹ በግለሰብ ተጠቃሚነት ላይ ሳይሆን በማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት የሚያደርጉ በመሆናቸው ከዘመናዊው የፍትህ ስርዓት በይበልጥ ለአብሮነት መጠናከር አስተዋጽኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹም ለሀገራዊ መግባባት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ፥ እሴቶቹ ተጠብቀው፣ ለምተውና ጎልብተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት እንደሚገባም መክረዋል። ሀገራችን ቂምና ቁርሾን የወለዱ ያለመግባባቶች በዘላቂነት በሰለጠነና ሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ሁሉንም ያሳተፈ ስራ እየሰራች እንደሆነ ያነሱት መምህርና ተመራማሪው አጎናፍር ሰለሞን ዕሴቶቹ በማህበረሰቡ ዘንድ ካላቸው ተቀባይነት እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ሂደቱን ከማገዝ አንጻር ጉልህ ሚና ስለሚኖራቸው መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል።