ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አዳማ ከተማ አሸንፈዋል 
Feb 21, 2026 23
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ20ኛ ሳምንት ሁለት ጨዋታዎች ማምሻውን ተደርገዋል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን 3 ለ 1 አሸንፏል። ዩጋንዳዊው ሳይመን ፒተር፣ ሁዘይፋ ሻፊ እና ሳምሶን ቹቹ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ታምራት እያሱ ለፋሲል ከነማ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ24 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ፋሲል ከነማ በ33 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሌላኛው መርሐ-ግብር አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አምበሉ ቢንያም አይተን በ61ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ አዳማ ከተማ በ31 ነጥብ አምስተኛ፣ የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ20 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዘዋል። ቀን ላይ በተደረጉ የ20ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3፣ ባህርዳር ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፈዋል።
የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ ነው
Feb 21, 2026 38
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢዲ ኮኔክት ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የ2026 የኢትዮ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ሳይንስ እና የትምህርት ፌስቲቫል ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።   ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ የመክፈቻ መርሐ ግብር ላይ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮችና ተማሪዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፤ በዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን ወጣቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለሀገሪቱ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ መሠረት መሆኑን ጠቁመው ፌስቲቫሉ ወጣቶች በትምህርት ልቀውና በሳይንስ መሪ መሆን እንዲችሉ ዓለም አቀፍ ልምድ ካላቸው ተቋማት ጋር ምህዳር እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ ከአጋር አካላት ጋር በመሆን የወጣቶችን የፈጠራ ስራ የሚያጎለብት "የሰመር ካምፕ" ለማዘጋጀት ማቀዱን ይፋ አድርገዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው፣ የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሰው ሀብት ልማት ላይ መስራት ቀዳሚ ተግባር ነው ብለዋል፡፡   ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ሥራዎች እንደ አማራጭ የሚታዩ ሳይሆን ለዘመናዊ ስልጣኔ መሰረት የሆኑ የልማት ምሰሶዎች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። የአፍሪካ ህብረት የጤና፣ ሰብአዊ መብቶች እና ማህበራዊ ልማት ኮሚሽነር አምባሳደር ሚንአታ ሳማቴ ሴሱማ፣ የወጣቶች ተሳትፎ ለአጀንዳ 2063 ስኬት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የዩኔስኮ የሰላም ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ጋይ ጆከን በበኩላቸው አፍሪካ ያላትን የወጣት ኃይል ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ እንደ ትልቅ ስትራቴጂካዊ ሀብት ሊወሰድ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢድ ኮኔክት ኢትዮጵያ መስራች ኢንጂነር ሳሙኤል ንጉሴ እንዳሉትም፤ ተቋማቸው ተማሪዎችን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሰራል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ የታደሙት ተማሪ ካይረን ግርማ እና ሲፈን ዮሃንስ በበኩላቸው፣ መድረኩ የትምህርት ዕድሎችን ለማግኘትና ዓለም አቀፍ እውቀትን ለመቅሰም ትልቅ በር እንደከፈተላቸው መስክረዋል። ፌስቲቫሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገውን የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ግቦች ከማሳካት አንጻር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል።
መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል
Feb 21, 2026 39
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን መገናኛ ብዙኃን የተጣለባቸውን አገራዊ ኃላፊነት በላቀ ደረጃ ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን፤የፖለቲካ ፓርቲዎችም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያዘጋጀውን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብ ፈርመዋል።፡፡   የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ምርጫውን ለማካሄድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናክሮ ቀጥሏል። መራጮች የሚፈልጉትን ፓርቲ ለይተው እንዲመርጡ የሚያስችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክቶች ዛሬ ይፋ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ አብዛኛዎቹ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ማስመዝገባቸውን ጠቁመው፤ ቀጣዩን የመራጮች ምዝገባ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ጠቁመዋል። የምርጫ አስፈጻሚዎችና መራጮችን ለሚያስተምሩ 169 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላት ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበው፤ በተለይም መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፍትሃዊነት በማስተናገድ አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን ለሕዝብ በማስተዋወቅ ረገድ ቦርዱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ በበኩላቸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፈረሙት የሥነ-ምግባር ደንብ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።   በዚህም ደንቡ ዋና ዋና የዲሞክራሲ መርሆዎችን ያካተተ መሆኑን ጠቅሰው፤ በማንኛውም የቅስቀሳ ወቅት መደለያ ከመጠቀም ወይም ኃይልን መሠረት ካደረገ እንቅስቃሴ መቆጠብ ግዴታ ነው ብለዋል። የዜጎችን ሰላም የሚያናጋ፣ ግጭት የሚቀሰቅስ ወይም ለአመጽ የሚጋብዝ ንግግር ማድረግ ፍጹም የተከለከለ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ከቦርዱ ዕውቅና ውጭ የምርጫ ውጤት ትንበያ መሥራት የተከለከለ ሲሆን፤ ማንኛውም ቅሬታ ያለው አካል በሕግ የተቀመጡ አሰራር ሥርዓቶችን ብቻ የመከተል ግዴታ አለበትም ብለዋል። በዛሬው መርሃ ግብር ላይ የቦርዱ የሥራ አመራር አባላት፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን፣ ሁሉም አካላት ለምርጫው ስኬታማነት በጋራ ለመሥራት ስምምነታቸውን በፊርማቸው አረጋግጠዋል።
በመርሃ ግብሩ ታቅፈን በትጋት ሰርተን በመቆጠባችን ከተረጂነት ለመውጣት ችለናል-ተጠቃሚዎች
Feb 21, 2026 44
ድሬደዋ ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- በሴፍትኔት መርሃ ግብር ታቅፈው በትጋት ሰርተው በመቆጠባቸው ከተረጂነት ለመውጣት መቻላቸውን የድሬዳዋ የሚገኙ ሴት የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚዎች ተናገሩ። በከተሞች ተግባራዊ የተደረገው የልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጥሪት እንዲያፈሩ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። የሴፍትኔት ፕሮግራም በከተሞች የሚታየውን ሥራ አጥነትና ስር የሰደደ ድህነት በመቀነስ በኩልም የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የተለያዩ ተጠቃሚዎች ይገልፃሉ ። መርሃ ግብሩ በከተሞች ዜጎች የምግብ ዋስትናቸውን በሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የራሳቸው ገቢ እንዲኖራቸውና የቁጠባ ባህላቸውን እንዲያጎለብቱ የሚያግዝ ነው። በድሬዳዋ አስተዳደር የሴፍትኔት ተጠቃሚ የነበሩ ሴቶች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በሴፍትኔት መርሃ ግብሩ ጠንክረው በመስራትና ጥሪት በመቋጠር ወደ ሌሎች የልማት ስራዎች ለመሻገር መቻላቸውን ገልጸዋል።   በመርሃ ግብሩ ተሳትፎ ማድረጋቸው ተጠቃሚነታቸውን ለማጎልበት ማስቻሉን አመልክተው ከዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ በመውጣት የራሳቸውን መኖሪያ ቤት ለመገንባት እንደቻሉ በመጠቆም። በመርሃ ግብሩ በመታቀፍ ከተረጂነት ለመውጣት እንደቻሉ የተናገሩት ወይዘሮ እታገኝ በለጠ እና ወይዘሮ አበባ ኃይሌ እንዳሉት፤ በሴፍትኔት መርሃ ግብር ታቅፈን በትጋት በመስራታችን ከተረጂነት ለመውጣት ችለናል።   በተለይ ለሴቶች በንግድ ስራና በክህሎት ማሳደግ ላይ የተሰጠው ስልጠና አዋጪ በሆነ የገቢ ማግኛ ስራ ላይ በመሰማራት ከተረጂነት ለመውጣት ያስቻለና ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የመፍጠር እድልንም ፈጥሮልናል ብለዋል። መንግስት ተግባራዊ ባደረገው የሴፍቲኔት መርሃ ግብር በመሳተፍ ባገኘሁት ድጋፍና ስልጠና ራሴን ከመቻል ባለፈ የቁጠባ ሒሳብ ለመክፈትና ገንዘብ ለማስቀመጥ ችያለሁ ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ከዲጃ ኢብሮ ናቸው።   ከዚህ ባለፈም ልጆቻቸውንም በተገቢው መንገድ ለማስተማር መቻላቸውንም ነው የገለፁት።   በድሬዳዋ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅህፈት ቤት የከተማ ምግብ ዋስትና ዳይሬክተር አቶ አብዱልሰላም መድህኔ፤ መንግስት ተረጂነትን የሚጠየፍ ትውልድ ለማፍራት እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራት በውጤት እየታጀቡ መሆኑን ገልጸዋል። ከእነዚህ ሰው ተኮር የልማት እንቅስቃሴዎች ጎን ለጎን የሚደረጉ የገንዘብ ድጋፍና የሙያ ስልጠናዎች በድህነት ውስጥ የሚገኙ ሴቶችን ወደ አምራችነት እያሸጋገሩ መሆናቸውን በመግለፅ። በድሬዳዋ ከተማም በሴፍትኔት መርሃ ግብር ተጠቃሚ የሆኑ 340 የሚደርሱ ሴቶች በቆጠቡትና በተደረገላቸው የገንዘብ ድጋፍ በመታገዝ በተለያዩ የገቢ ማግኛ ስራዎች ላይ በመሰማራት ከተረጂነት ወደ አምራችነት መሸጋገራቸውን ነው የገለጹት።
የሚታይ
የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ ነው
Feb 21, 2026 38
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢዲ ኮኔክት ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የ2026 የኢትዮ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ሳይንስ እና የትምህርት ፌስቲቫል ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።   ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ የመክፈቻ መርሐ ግብር ላይ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮችና ተማሪዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፤ በዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን ወጣቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለሀገሪቱ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ መሠረት መሆኑን ጠቁመው ፌስቲቫሉ ወጣቶች በትምህርት ልቀውና በሳይንስ መሪ መሆን እንዲችሉ ዓለም አቀፍ ልምድ ካላቸው ተቋማት ጋር ምህዳር እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ ከአጋር አካላት ጋር በመሆን የወጣቶችን የፈጠራ ስራ የሚያጎለብት "የሰመር ካምፕ" ለማዘጋጀት ማቀዱን ይፋ አድርገዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው፣ የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሰው ሀብት ልማት ላይ መስራት ቀዳሚ ተግባር ነው ብለዋል፡፡   ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ሥራዎች እንደ አማራጭ የሚታዩ ሳይሆን ለዘመናዊ ስልጣኔ መሰረት የሆኑ የልማት ምሰሶዎች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። የአፍሪካ ህብረት የጤና፣ ሰብአዊ መብቶች እና ማህበራዊ ልማት ኮሚሽነር አምባሳደር ሚንአታ ሳማቴ ሴሱማ፣ የወጣቶች ተሳትፎ ለአጀንዳ 2063 ስኬት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የዩኔስኮ የሰላም ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ጋይ ጆከን በበኩላቸው አፍሪካ ያላትን የወጣት ኃይል ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ እንደ ትልቅ ስትራቴጂካዊ ሀብት ሊወሰድ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢድ ኮኔክት ኢትዮጵያ መስራች ኢንጂነር ሳሙኤል ንጉሴ እንዳሉትም፤ ተቋማቸው ተማሪዎችን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሰራል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ የታደሙት ተማሪ ካይረን ግርማ እና ሲፈን ዮሃንስ በበኩላቸው፣ መድረኩ የትምህርት ዕድሎችን ለማግኘትና ዓለም አቀፍ እውቀትን ለመቅሰም ትልቅ በር እንደከፈተላቸው መስክረዋል። ፌስቲቫሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገውን የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ግቦች ከማሳካት አንጻር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል።
መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል
Feb 21, 2026 39
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን መገናኛ ብዙኃን የተጣለባቸውን አገራዊ ኃላፊነት በላቀ ደረጃ ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን፤የፖለቲካ ፓርቲዎችም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያዘጋጀውን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብ ፈርመዋል።፡፡   የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ምርጫውን ለማካሄድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናክሮ ቀጥሏል። መራጮች የሚፈልጉትን ፓርቲ ለይተው እንዲመርጡ የሚያስችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክቶች ዛሬ ይፋ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ አብዛኛዎቹ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ማስመዝገባቸውን ጠቁመው፤ ቀጣዩን የመራጮች ምዝገባ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ጠቁመዋል። የምርጫ አስፈጻሚዎችና መራጮችን ለሚያስተምሩ 169 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላት ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበው፤ በተለይም መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፍትሃዊነት በማስተናገድ አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን ለሕዝብ በማስተዋወቅ ረገድ ቦርዱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ በበኩላቸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፈረሙት የሥነ-ምግባር ደንብ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።   በዚህም ደንቡ ዋና ዋና የዲሞክራሲ መርሆዎችን ያካተተ መሆኑን ጠቅሰው፤ በማንኛውም የቅስቀሳ ወቅት መደለያ ከመጠቀም ወይም ኃይልን መሠረት ካደረገ እንቅስቃሴ መቆጠብ ግዴታ ነው ብለዋል። የዜጎችን ሰላም የሚያናጋ፣ ግጭት የሚቀሰቅስ ወይም ለአመጽ የሚጋብዝ ንግግር ማድረግ ፍጹም የተከለከለ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ከቦርዱ ዕውቅና ውጭ የምርጫ ውጤት ትንበያ መሥራት የተከለከለ ሲሆን፤ ማንኛውም ቅሬታ ያለው አካል በሕግ የተቀመጡ አሰራር ሥርዓቶችን ብቻ የመከተል ግዴታ አለበትም ብለዋል። በዛሬው መርሃ ግብር ላይ የቦርዱ የሥራ አመራር አባላት፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን፣ ሁሉም አካላት ለምርጫው ስኬታማነት በጋራ ለመሥራት ስምምነታቸውን በፊርማቸው አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ ሀገር ያጸኑ ጀግኖች ምድር ናት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 
Feb 21, 2026 72
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር ያጸኑ የበርካታ ጀግኖች ምድር ናት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ተጠናቀቀ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር ያጸኑ የበርካታ ጀግኖች ምድር መሆኗን አስገንዝበዋል።   የመከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች እዝም ባለፉት 65 ዓመታት በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ የማይበገር ጽናት ይዞ ኢትዮጵያን ያኮራ ጀብዱ ፈጽሟል ብለዋል። እዙ አሁን ላይ በመከላከያ ሪፎርም ስራዎች አማካኝነት አየር ወለድ፣ ኮማንዶ እና ልዩ የጸረ ሽብር ኃይል መያዙንም አመላክተዋል። በዚህም መሠረት በአደረጃጀት፣ በሰው ኃይል እና በትጥቅ ዘመኑን በዋጀ መልኩ መዋቀሩን ነው ያስታወቁት።   በመሆኑም በየትኛውም ጊዜና በማንኛውም ሁኔታ እዙ ግዳጁን በብቃት ለመፈጸም በአስተማማኝ ቁመና ላይ ይገኛል ሲሉ አረጋግጠዋል። ‎ እዙ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ሲያከብር የገነባውን የዘመነ ወታደራዊ አቅም፣ የሰው ኃይል ዝግጁነት እና የታክቲክ ብቃት ለሕዝብ ይፋ አድርጓል ብለዋል።   በተለይም ዛሬ የቀረበው የተቀናጀ የውሃ ላይ ልምምድ፣ የአየር ወለድና የኮማንዶ አባላት በቅንጅት ያሳዩት ልዩ ልዩ ወታደራዊ ክህሎት የሠራዊቱን ከፍተኛ ብቃት ያረጋገጠ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የመንግስት የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው 
Feb 21, 2026 90
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የመንግስት የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ቢሮ ያዘጋጀው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያ ታምርት ኤግዚቢሽንና ባዛር የመክፈቻ መርኃ ግብር እየተካሄደ ነው። አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ውጤታማ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኙ ነው በመርኃ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እና ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን ተገኝተዋል።   ለአንድ ሳምንት የሚቆየው ኤግዚቢሽንና ባዛር "ኢትዮጵያ ታምርት፤ አዲስ አበባ ትበልፅግ" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተከፍቷል፡፡ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መንግሥት የአምራች ዘርፉን የሀገር ሉዓላዊነትና የጠንካራ መንግሥት መገለጫ አድርጎ ይመለከተዋል፡፡ አባቶቻችን የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ነጻነት ለማስከበር ዓድዋ ላይ ያስመዘገቡትን ጀብዱ መንግስት በኢኮኖሚው መስክ ለመድገም ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ለዚህ ስኬት ቁልፍ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ከማድረግ ጀምሮ የዘርፉን እድገት የሚያሳልጡ የተለያዩ ኢንሼቲቮችን ገቢራዊ አድርጓል ብለዋል፡፡   የአምራች ዘርፉ የጠንካራ ኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን በማንሳት፤ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ወሳኝ ርምጃዎች የአምራች ኢንዱስትሪው ሀገር አቀፍ የማምረት አቅም አጠቃቀም 66 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን አስታውቀዋል። በዚህም በኢትዮጵያ የሚመረቱ በርካታ ምርቶች ለታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች በግብዓትነት እያገለገሉ መሆኑን ገልጸው፤ አፈጻጸሙን ከዚህ በላይ ለማሳደግ መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዕድገት ከኢንዱስትሪ ዕድገት ጋር በእጅጉ የተሳሰረ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ከተማዋ የማምረቻ ማዕከል እንድትሆን በቅንጅት እንደሚሠራ ተናግረዋል፡፡ የምርቶችን ጥራት፣ መጠንና ብዝሃነት በማሳደግ በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ማድረግ፣ የፈጠራ ሥራዎችን በማበረታታት የማምረቻ መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ማጎልበት የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ የአምራች ዘርፉ ተዋንያን አጋርነታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቀርበዋል፡፡
አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ውጤታማ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኙ ነው
Feb 21, 2026 62
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ውጤታማ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኙ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ቢሮ ያዘጋጀው ከተማ አቀፍ የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ኤግዚቢሽንና ባዛር በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የመክፈቻ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡ የመንግስት የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው “ኢትዮጵያ ታምርት፤ አዲስ አበባ ትበልፅግ” በሚል መሪ ሀሳብ በተሰናዳው በዚህ መርኃግብር ላይ የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ለሀገር ሉዓላዊነት መከበርና ለብልፅግና መረጋገጥ መሰረታዊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ከንቲባዋ፤ በተለይም ከለውጡ ወዲህ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች አበረታች መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሁሉን አቀፍ የለውጥ ጉዞ የሚሰምረው ምርትና ምርታማነት ሲያድግ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ ይህንንም አሁን ላይ በተጨባጭ በውጤት እያየነው እንገኛለን ብለዋል፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የመዲናዋ ቀዳሚ የትኩረት መስክ መሆኑን ገልጸው፤ ለዘርፉ እድገት እንቅፋት የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት አስተዳደሩ በቁርጠኝነት ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል።   ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል ለኢንዱስትሪዎች የሚሆን የመስሪያ ቦታን ማመቻቸት፣ አምራቾች የገንዘብ አቅርቦት እንዲያገኙ ድጋፍ ማድረግ እንዲሁም የፈጠራ ባለቤቶችን በመደገፍ የዘርፉን ተግዳሮቶች መቅረፍ ለአብነት አንስተዋል፡፡ አስተዳደሩ ፈጣንና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ሚና የማሳደግ እቅድ ይዞ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ በመጪዎቹ ዓመታት ዘርፉ የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት እንዲሆን የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው፤ በከተማዋ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት በሙሉ ሁለንተናዊ ለውጥን ዓላማ ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በከተማዋ የሚገኙ አምራቾች የሀገር ውስጥ ግብዓት አጠቃቀማቸው 45 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፤ ይህም የዜጎችን የሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀም ባህል በከፍተኛ ደረጃ እየለወጠው መሆኑን ገልጸዋል።   በመዲናዋ 3 ሺህ 890 የሚደርሱ ኢንዱስትሪዎች እንደሚገኙና እነዚህም ለከተማዋ የኢኮኖሚ እድገት የላቀ ድርሻ እያበረከቱ መሆኑን አስረድተዋል። ይህ ንቅናቄ ምርትን ከማስተዋወቅ ባለፈ በአምራች ዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በመለየት ረገድ ችግር ፈቺ መፍትሔዎችን እያመጣ እንደሚገኝና ለዘርፉ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። አዲስ አበባ ሁሉም ኢንዱስትሪዎች በስፋት የሚያብቡባት ማዕከል እንድትሆን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። መንግስት የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነት ለማሳደግና የከተማዋን የኢኮኖሚ መዋቅር ስር ነቀል በሆነ መልኩ ለመቀየር የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ይህ ለአንድ ሳምንት የሚቆየው ኤግዚቢሽንና ባዛር የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለህዝብ ከማስተዋወቅ ባለፈ፣ በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ሰፊ የገበያ ትስስር እንደሚፈጥር ይጠበቃል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል
Feb 21, 2026 39
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን መገናኛ ብዙኃን የተጣለባቸውን አገራዊ ኃላፊነት በላቀ ደረጃ ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን፤የፖለቲካ ፓርቲዎችም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያዘጋጀውን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብ ፈርመዋል።፡፡   የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ምርጫውን ለማካሄድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናክሮ ቀጥሏል። መራጮች የሚፈልጉትን ፓርቲ ለይተው እንዲመርጡ የሚያስችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክቶች ዛሬ ይፋ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ አብዛኛዎቹ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ማስመዝገባቸውን ጠቁመው፤ ቀጣዩን የመራጮች ምዝገባ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ጠቁመዋል። የምርጫ አስፈጻሚዎችና መራጮችን ለሚያስተምሩ 169 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላት ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበው፤ በተለይም መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፍትሃዊነት በማስተናገድ አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን ለሕዝብ በማስተዋወቅ ረገድ ቦርዱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ በበኩላቸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፈረሙት የሥነ-ምግባር ደንብ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።   በዚህም ደንቡ ዋና ዋና የዲሞክራሲ መርሆዎችን ያካተተ መሆኑን ጠቅሰው፤ በማንኛውም የቅስቀሳ ወቅት መደለያ ከመጠቀም ወይም ኃይልን መሠረት ካደረገ እንቅስቃሴ መቆጠብ ግዴታ ነው ብለዋል። የዜጎችን ሰላም የሚያናጋ፣ ግጭት የሚቀሰቅስ ወይም ለአመጽ የሚጋብዝ ንግግር ማድረግ ፍጹም የተከለከለ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ከቦርዱ ዕውቅና ውጭ የምርጫ ውጤት ትንበያ መሥራት የተከለከለ ሲሆን፤ ማንኛውም ቅሬታ ያለው አካል በሕግ የተቀመጡ አሰራር ሥርዓቶችን ብቻ የመከተል ግዴታ አለበትም ብለዋል። በዛሬው መርሃ ግብር ላይ የቦርዱ የሥራ አመራር አባላት፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን፣ ሁሉም አካላት ለምርጫው ስኬታማነት በጋራ ለመሥራት ስምምነታቸውን በፊርማቸው አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ ሀገር ያጸኑ ጀግኖች ምድር ናት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 
Feb 21, 2026 72
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር ያጸኑ የበርካታ ጀግኖች ምድር ናት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ተጠናቀቀ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር ያጸኑ የበርካታ ጀግኖች ምድር መሆኗን አስገንዝበዋል።   የመከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች እዝም ባለፉት 65 ዓመታት በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ የማይበገር ጽናት ይዞ ኢትዮጵያን ያኮራ ጀብዱ ፈጽሟል ብለዋል። እዙ አሁን ላይ በመከላከያ ሪፎርም ስራዎች አማካኝነት አየር ወለድ፣ ኮማንዶ እና ልዩ የጸረ ሽብር ኃይል መያዙንም አመላክተዋል። በዚህም መሠረት በአደረጃጀት፣ በሰው ኃይል እና በትጥቅ ዘመኑን በዋጀ መልኩ መዋቀሩን ነው ያስታወቁት።   በመሆኑም በየትኛውም ጊዜና በማንኛውም ሁኔታ እዙ ግዳጁን በብቃት ለመፈጸም በአስተማማኝ ቁመና ላይ ይገኛል ሲሉ አረጋግጠዋል። ‎ እዙ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ሲያከብር የገነባውን የዘመነ ወታደራዊ አቅም፣ የሰው ኃይል ዝግጁነት እና የታክቲክ ብቃት ለሕዝብ ይፋ አድርጓል ብለዋል።   በተለይም ዛሬ የቀረበው የተቀናጀ የውሃ ላይ ልምምድ፣ የአየር ወለድና የኮማንዶ አባላት በቅንጅት ያሳዩት ልዩ ልዩ ወታደራዊ ክህሎት የሠራዊቱን ከፍተኛ ብቃት ያረጋገጠ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብን ፈረሙ
Feb 21, 2026 77
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያዘጋጀውን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብ ፈረሙ። ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ አደረገ የስነ ምግባር ደንቡ ምርጫው ስነ ምግባርን በተላበሰ መልኩ በሰላማዊ መንገድ እንዲካሄድ የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል። በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የቦርዱ ስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች ተኝተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዚሁ ወቅት፥ ቦርዱ ፓርቲዎች ክርክር አድርገው አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝቡ የሚያቀርቡበት መር ሃግብር እየተዘጋጀ ነው ብለዋል። መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ ተመስርቶ ምርጫ እንዲያደርግ ከፓርቲዎች ብዙ ስራ ይጠበቃል ያሉት ሰብሳቢዋ፥ መገናኛ ብዙኃንም ለተወዳዳሪ ፓርቲዎች እኩል የአየር ሰዓት በመመደብ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አመልክተዋል። ምርጫ ቦርድም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የኢዜአ የዲጂታል ሚዲያ ገጾች https://linktr.ee/ENADigital
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል
Feb 21, 2026 69
ሚዛን አማን፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን በቤንች ሸኮ ዞን ኢዜአ ያነጋገራቸው ሴቶች ተናገሩ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሻለ ሀሳብ ማቅረብ ላይ በማተኮር የሀገሪቱን የዴሞክራሲ ልምምድ ማጠናከር እንደሚገባቸውም ተገልጿል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የትግራይ ክልል ሕዝብ ይበጁኛል የሚላቸውን ወኪሎቹ በነፃነት ለመምረጥ የሚያስችለው ወሳኝ መድረክ ነው ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ አደረገ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሔደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል። የምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ሚና ካላቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች መካከል ሴቶች ዋነኞቹ ናቸው። በቤንች ሸኮ ዞን የሚዛን አማን ነዋሪ የሆኑት መምህርት ትዕግሥት ኡኩሞ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምርጫ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ይበጀናል ያልነውን የምንወክልበት በመሆኑ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል ብለዋል።   ለዚህም ለሀገር ልማት፣ ለሴቶች ሁለተናዊ ተጠቃሚነት የሚሰራ ተፎካካሪ ፓርቲን በነፃነት ለመምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን ነው የሚገልጹት። ዘንድሮ ኢትዮጵያ የምታካሂደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም ሴቶች ከቤተሰብ ጀምሮ ያለንን ሚና ማጠናከር ይጠበቅብናል ነው ያሉት። የመራጮች የምዝገባ ቀንን በጉጉት እየጠበቁ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ዘሪቱ በቀለ ናቸው።   ምርጫ የዲሞክራሲ ልምድን የሚያጎለብት በመሆኑ እኔም ሆንኩ ቤተሰቤ ሀገርን ወደ ተሻለ እድገት የሚወስድ ፓርቲን ለመምረጥ የነቃ ተሳትፎ እናደርጋለን ነው ያሉት። ከምንም ነገር በፊት ቀዳሚ መሆን ያለበት የሀገር ሰላም በመሆኑ ሴቶች በየአካባቢያችን የተረጋጋ የፖለቲካ እንቅስቃሴ እንዲኖር እንሰራለን ነው ያሉት። ፍትሐዊና ነጻ ምርጫ ማካሔድ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት መከበርና ገጽታ ግንባታ ትልቅ ሚና እንዳለው በመረዳት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሀገርን እያሰቡ ሊሰሩ እንደሚገባም አመልክተዋል።   የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ መሰለች ፍቃዱ፤ ሴቶች መንግስት በፖለቲካ ዘርፍ እኩል ተሳታፊ እንዲሆኑ የፈጠረላቸውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በምርጫው ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ አደረገ
Feb 21, 2026 132
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ አደረገ። ቦርዱ የዕጩዎች ስነ ምግባር ደንብ መፈረሚያ መርሐ ግብርም እያካሄደ ሲሆን፤ በመርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራር እና አባላት እንዲሁም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ተወካዮች ተገኝተዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቦርዱ ምርጫውን ለማካሄድ እያደረገ ያለውን ዝግጅት አጠናክሮ ቀጥሏል። አብዛኛዎቹ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎችን ማስመዝገባቸውን ገልጸው፤ የመራጮች ምዝገባ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የምርጫ አስፈጻሚዎች የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው፤ የመራጮች ትምህርት ለሚሰጡ 169 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችም ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል። የምርጫ ቁሳቁስ ዝግጅት ያለበትን ደረጃ ቦርዱ ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ማስጎበኘቱንም ጠቅሰዋል። በዛሬው ዕለት ይፋ የተደረገው የፓርቲዎች የምርጫ ምልክት መራጮች የሚፈልጉትን ፓርቲ ምልክት አውቀው እንዲመርጡ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል። ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ እንዲሆን የዕጩዎች የሥነ-ምግባር ደንብ የተዘጋጀ መሆኑን አመልክተው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መመሪያውን እንደሚፈርሙ ተናግረዋል። ምርጫው ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲካሄድ ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባም አመልክተዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የትግራይ ክልል ሕዝብ ይበጁኛል የሚላቸውን ወኪሎቹ በነፃነት ለመምረጥ የሚያስችለው ወሳኝ መድረክ ነው
Feb 21, 2026 65
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የትግራይ ክልል ሕዝብ ይበጁኛል የሚላቸውን ወኪሎቹን በነፃነት ለመምረጥ የሚያስችለው ወሳኝ መድረክ መሆኑን የስምረት ፓርቲ ምክር ቤት አባል ሽሻይ አማረ (ዶ/ር) ገለጹ። የትግራይ ሕዝብ ከለውጡ ጋር እንዳይራመድ በተጽዕኖ ውስጥ እንዲቆይ መደረጉ ለዓመታት ዋጋ አስከፍሎታል ሲሉም ሽሻይ አማረ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ጊዜያዊ አስተዳደር ተቋቁሞ የክልሉ ሕዝብ የተረጋጋና ሰላማዊ ሁኔታ ውስጥ እንዲገባ መደረጉ መጠነኛ ለውጥ እንዲመጣ ማድረጉን አመልክተዋል። በዚህ ዓመት በሚካሔደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ሕዝቡ በነጻነት ወጥቶ መምረጥ እንደሚፈልግ ገልጸው፤ ለዚህም በክልሉ አካታችና አሳታፊ የሆነ ምርጫ ሊካሔድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ለዚህም የሚመለከታቸው አካላት በልዩ ትኩረት በርብርብ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። በምርጫ ቦርድ ሕጋዊ ዕውቅና የሌለው የሕወሃት ቡድን በትግራይ ክልል ምርጫ እንዳይካሔድ ፍላጎት እንዳለው ጠቁመው፤ ይህ ሁኔታ በሕጋዊ አግባብ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል ብለዋል። ምርጫው እንዲከናወን የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ ለክልሉ ሕዝብ ትልቅ እፎይታ የሚሰጥ መሆኑን አንስተዋል። ይህም የትግራይ ሕዝብ ለሚያነሳው ጥያቄ ፍትሐዊ ምላሽ እንዲያገኝና ተደማጭ እንዲሆን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አብራርተዋል። ሌላው በኢትዮጵያ በሂደት ላይ ያለው ሀገራዊ ምክክር የሁሉንም ዜጎች ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ታሳቢ ባደረገ መልኩ መቋቋሙ በየአካባቢው ለሚከሰቱና አግባብነት ለሌላቸው ልዩነቶች ምላሽ የሚሰጥ ነው ብለዋል። በተለይም ለትግራይ ሕዝብ ብዙ ዕድሎችን ይዞ የሚመጣ ትልቅ መፍትሔ ስለመሆኑም አስረድተዋል።   ሀገራዊ የምክክር ሒደቱ አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን አመልክተው፤ የትግራይ ሕዝብ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ አጀንዳውን ማውጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የዕዙ አኩሪ የጀግንነት ታሪኮች ተጽፈው አያልቁም - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Feb 20, 2026 131
ሐዋሳ፤ የካቲት 13/2018 (ኢዜአ)፡- የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ተጽፈው የማያልቁ በርካታ አኩሪ የጀግንነት ታሪኮች አሉት ሲሉ የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው ''የውጊያ ማርሽ ቀያሪዎቹ'' በሚል ርዕስ የተፃፈው መጽሐፍ ዛሬ በሐዋሳ ተመርቋል።   ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚሁ ወቅት፤ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የተፈጸሙ የጀግንነት ጀብዱዎች ተነግረው የማያልቁ ናቸው ብለዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝም በመጽሐፍ ተጽፈው የማያልቁ አኩሪ የጀግንነት ታሪኮች እንዳሉት ጠቅሰው፤ ይህን የጀግንነት ታሪክም ለቀጣዮቹ ጀግኖች በአግባቡ ሠንዶ ማስቀመጥ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሀገር ዳር ድንበርንና ሉዓላዊነትን ለማስከበር ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለ፣ ሀገርና ሕዝብ የሚኮሩበት ታሪክ የሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል። ''የውጊያ ማርሽ ቀያሪዎቹ'' መጽሐፍ በስድስት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን፤ የዕዙ ታሪኮችን በ526 ገጾቹ ያስቃኛል።   በዚህም መሠረት፤ የልዩ ዘመቻዎች ኃይል በኢትዮጵያ፣ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የአሁን ተጋድሎ ታሪክ፣ ድንበር ያልገደበው የጀግንነት ውሎ፣ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ቀደምት የተጋድሎ ታሪክ፣ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝና ሕብረተሰብ እንዲሁም የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የነገ ትልም በሚሉ ርዕሶች በየምዕራፉ ዝርዝር ሐሳቦችን ይዟል። መጽሐፉ ዕዙ ከተመሰረተበት ከ1953 ዓ.ም ጀምሮ እስከአሁን ያሉትን የ65 ዓመታት የተጋድሎ ታሪክ በፎቶ አስደግፎ መያዙም ተመላክቷል።
ፖለቲካ
መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል
Feb 21, 2026 39
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን መገናኛ ብዙኃን የተጣለባቸውን አገራዊ ኃላፊነት በላቀ ደረጃ ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ይፋ ያደረገ ሲሆን፤የፖለቲካ ፓርቲዎችም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያዘጋጀውን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብ ፈርመዋል።፡፡   የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ምርጫውን ለማካሄድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናክሮ ቀጥሏል። መራጮች የሚፈልጉትን ፓርቲ ለይተው እንዲመርጡ የሚያስችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክቶች ዛሬ ይፋ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ አብዛኛዎቹ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ማስመዝገባቸውን ጠቁመው፤ ቀጣዩን የመራጮች ምዝገባ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ጠቁመዋል። የምርጫ አስፈጻሚዎችና መራጮችን ለሚያስተምሩ 169 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላት ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበው፤ በተለይም መገናኛ ብዙኃን ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፍትሃዊነት በማስተናገድ አገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን ለሕዝብ በማስተዋወቅ ረገድ ቦርዱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ በበኩላቸው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፈረሙት የሥነ-ምግባር ደንብ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።   በዚህም ደንቡ ዋና ዋና የዲሞክራሲ መርሆዎችን ያካተተ መሆኑን ጠቅሰው፤ በማንኛውም የቅስቀሳ ወቅት መደለያ ከመጠቀም ወይም ኃይልን መሠረት ካደረገ እንቅስቃሴ መቆጠብ ግዴታ ነው ብለዋል። የዜጎችን ሰላም የሚያናጋ፣ ግጭት የሚቀሰቅስ ወይም ለአመጽ የሚጋብዝ ንግግር ማድረግ ፍጹም የተከለከለ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ከቦርዱ ዕውቅና ውጭ የምርጫ ውጤት ትንበያ መሥራት የተከለከለ ሲሆን፤ ማንኛውም ቅሬታ ያለው አካል በሕግ የተቀመጡ አሰራር ሥርዓቶችን ብቻ የመከተል ግዴታ አለበትም ብለዋል። በዛሬው መርሃ ግብር ላይ የቦርዱ የሥራ አመራር አባላት፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን፣ ሁሉም አካላት ለምርጫው ስኬታማነት በጋራ ለመሥራት ስምምነታቸውን በፊርማቸው አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ ሀገር ያጸኑ ጀግኖች ምድር ናት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 
Feb 21, 2026 72
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር ያጸኑ የበርካታ ጀግኖች ምድር ናት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ተጠናቀቀ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር ያጸኑ የበርካታ ጀግኖች ምድር መሆኗን አስገንዝበዋል።   የመከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች እዝም ባለፉት 65 ዓመታት በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ የማይበገር ጽናት ይዞ ኢትዮጵያን ያኮራ ጀብዱ ፈጽሟል ብለዋል። እዙ አሁን ላይ በመከላከያ ሪፎርም ስራዎች አማካኝነት አየር ወለድ፣ ኮማንዶ እና ልዩ የጸረ ሽብር ኃይል መያዙንም አመላክተዋል። በዚህም መሠረት በአደረጃጀት፣ በሰው ኃይል እና በትጥቅ ዘመኑን በዋጀ መልኩ መዋቀሩን ነው ያስታወቁት።   በመሆኑም በየትኛውም ጊዜና በማንኛውም ሁኔታ እዙ ግዳጁን በብቃት ለመፈጸም በአስተማማኝ ቁመና ላይ ይገኛል ሲሉ አረጋግጠዋል። ‎ እዙ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ሲያከብር የገነባውን የዘመነ ወታደራዊ አቅም፣ የሰው ኃይል ዝግጁነት እና የታክቲክ ብቃት ለሕዝብ ይፋ አድርጓል ብለዋል።   በተለይም ዛሬ የቀረበው የተቀናጀ የውሃ ላይ ልምምድ፣ የአየር ወለድና የኮማንዶ አባላት በቅንጅት ያሳዩት ልዩ ልዩ ወታደራዊ ክህሎት የሠራዊቱን ከፍተኛ ብቃት ያረጋገጠ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብን ፈረሙ
Feb 21, 2026 77
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያዘጋጀውን የዕጩዎች የስነ ምግባር ደንብ ፈረሙ። ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ አደረገ የስነ ምግባር ደንቡ ምርጫው ስነ ምግባርን በተላበሰ መልኩ በሰላማዊ መንገድ እንዲካሄድ የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል። በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የቦርዱ ስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች ተኝተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዚሁ ወቅት፥ ቦርዱ ፓርቲዎች ክርክር አድርገው አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝቡ የሚያቀርቡበት መር ሃግብር እየተዘጋጀ ነው ብለዋል። መራጩ ህዝብ በእውቀት ላይ ተመስርቶ ምርጫ እንዲያደርግ ከፓርቲዎች ብዙ ስራ ይጠበቃል ያሉት ሰብሳቢዋ፥ መገናኛ ብዙኃንም ለተወዳዳሪ ፓርቲዎች እኩል የአየር ሰዓት በመመደብ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አመልክተዋል። ምርጫ ቦርድም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የኢዜአ የዲጂታል ሚዲያ ገጾች https://linktr.ee/ENADigital
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል
Feb 21, 2026 69
ሚዛን አማን፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን በቤንች ሸኮ ዞን ኢዜአ ያነጋገራቸው ሴቶች ተናገሩ። የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሻለ ሀሳብ ማቅረብ ላይ በማተኮር የሀገሪቱን የዴሞክራሲ ልምምድ ማጠናከር እንደሚገባቸውም ተገልጿል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የትግራይ ክልል ሕዝብ ይበጁኛል የሚላቸውን ወኪሎቹ በነፃነት ለመምረጥ የሚያስችለው ወሳኝ መድረክ ነው ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ አደረገ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሔደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል። የምርጫው ሂደት ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ሚና ካላቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች መካከል ሴቶች ዋነኞቹ ናቸው። በቤንች ሸኮ ዞን የሚዛን አማን ነዋሪ የሆኑት መምህርት ትዕግሥት ኡኩሞ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምርጫ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ይበጀናል ያልነውን የምንወክልበት በመሆኑ የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል ብለዋል።   ለዚህም ለሀገር ልማት፣ ለሴቶች ሁለተናዊ ተጠቃሚነት የሚሰራ ተፎካካሪ ፓርቲን በነፃነት ለመምረጥ የሚያስችላቸውን ካርድ ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን ነው የሚገልጹት። ዘንድሮ ኢትዮጵያ የምታካሂደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም ሴቶች ከቤተሰብ ጀምሮ ያለንን ሚና ማጠናከር ይጠበቅብናል ነው ያሉት። የመራጮች የምዝገባ ቀንን በጉጉት እየጠበቁ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ዘሪቱ በቀለ ናቸው።   ምርጫ የዲሞክራሲ ልምድን የሚያጎለብት በመሆኑ እኔም ሆንኩ ቤተሰቤ ሀገርን ወደ ተሻለ እድገት የሚወስድ ፓርቲን ለመምረጥ የነቃ ተሳትፎ እናደርጋለን ነው ያሉት። ከምንም ነገር በፊት ቀዳሚ መሆን ያለበት የሀገር ሰላም በመሆኑ ሴቶች በየአካባቢያችን የተረጋጋ የፖለቲካ እንቅስቃሴ እንዲኖር እንሰራለን ነው ያሉት። ፍትሐዊና ነጻ ምርጫ ማካሔድ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት መከበርና ገጽታ ግንባታ ትልቅ ሚና እንዳለው በመረዳት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሀገርን እያሰቡ ሊሰሩ እንደሚገባም አመልክተዋል።   የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ መሰለች ፍቃዱ፤ ሴቶች መንግስት በፖለቲካ ዘርፍ እኩል ተሳታፊ እንዲሆኑ የፈጠረላቸውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በምርጫው ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ አደረገ
Feb 21, 2026 132
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ አደረገ። ቦርዱ የዕጩዎች ስነ ምግባር ደንብ መፈረሚያ መርሐ ግብርም እያካሄደ ሲሆን፤ በመርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራር እና አባላት እንዲሁም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ተወካዮች ተገኝተዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቦርዱ ምርጫውን ለማካሄድ እያደረገ ያለውን ዝግጅት አጠናክሮ ቀጥሏል። አብዛኛዎቹ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎችን ማስመዝገባቸውን ገልጸው፤ የመራጮች ምዝገባ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የምርጫ አስፈጻሚዎች የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው፤ የመራጮች ትምህርት ለሚሰጡ 169 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችም ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል። የምርጫ ቁሳቁስ ዝግጅት ያለበትን ደረጃ ቦርዱ ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ማስጎበኘቱንም ጠቅሰዋል። በዛሬው ዕለት ይፋ የተደረገው የፓርቲዎች የምርጫ ምልክት መራጮች የሚፈልጉትን ፓርቲ ምልክት አውቀው እንዲመርጡ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል። ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ እንዲሆን የዕጩዎች የሥነ-ምግባር ደንብ የተዘጋጀ መሆኑን አመልክተው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መመሪያውን እንደሚፈርሙ ተናግረዋል። ምርጫው ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲካሄድ ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባም አመልክተዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የትግራይ ክልል ሕዝብ ይበጁኛል የሚላቸውን ወኪሎቹ በነፃነት ለመምረጥ የሚያስችለው ወሳኝ መድረክ ነው
Feb 21, 2026 65
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የትግራይ ክልል ሕዝብ ይበጁኛል የሚላቸውን ወኪሎቹን በነፃነት ለመምረጥ የሚያስችለው ወሳኝ መድረክ መሆኑን የስምረት ፓርቲ ምክር ቤት አባል ሽሻይ አማረ (ዶ/ር) ገለጹ። የትግራይ ሕዝብ ከለውጡ ጋር እንዳይራመድ በተጽዕኖ ውስጥ እንዲቆይ መደረጉ ለዓመታት ዋጋ አስከፍሎታል ሲሉም ሽሻይ አማረ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ጊዜያዊ አስተዳደር ተቋቁሞ የክልሉ ሕዝብ የተረጋጋና ሰላማዊ ሁኔታ ውስጥ እንዲገባ መደረጉ መጠነኛ ለውጥ እንዲመጣ ማድረጉን አመልክተዋል። በዚህ ዓመት በሚካሔደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ሕዝቡ በነጻነት ወጥቶ መምረጥ እንደሚፈልግ ገልጸው፤ ለዚህም በክልሉ አካታችና አሳታፊ የሆነ ምርጫ ሊካሔድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ለዚህም የሚመለከታቸው አካላት በልዩ ትኩረት በርብርብ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። በምርጫ ቦርድ ሕጋዊ ዕውቅና የሌለው የሕወሃት ቡድን በትግራይ ክልል ምርጫ እንዳይካሔድ ፍላጎት እንዳለው ጠቁመው፤ ይህ ሁኔታ በሕጋዊ አግባብ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል ብለዋል። ምርጫው እንዲከናወን የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ ለክልሉ ሕዝብ ትልቅ እፎይታ የሚሰጥ መሆኑን አንስተዋል። ይህም የትግራይ ሕዝብ ለሚያነሳው ጥያቄ ፍትሐዊ ምላሽ እንዲያገኝና ተደማጭ እንዲሆን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አብራርተዋል። ሌላው በኢትዮጵያ በሂደት ላይ ያለው ሀገራዊ ምክክር የሁሉንም ዜጎች ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ታሳቢ ባደረገ መልኩ መቋቋሙ በየአካባቢው ለሚከሰቱና አግባብነት ለሌላቸው ልዩነቶች ምላሽ የሚሰጥ ነው ብለዋል። በተለይም ለትግራይ ሕዝብ ብዙ ዕድሎችን ይዞ የሚመጣ ትልቅ መፍትሔ ስለመሆኑም አስረድተዋል።   ሀገራዊ የምክክር ሒደቱ አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን አመልክተው፤ የትግራይ ሕዝብ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ አጀንዳውን ማውጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የዕዙ አኩሪ የጀግንነት ታሪኮች ተጽፈው አያልቁም - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
Feb 20, 2026 131
ሐዋሳ፤ የካቲት 13/2018 (ኢዜአ)፡- የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ተጽፈው የማያልቁ በርካታ አኩሪ የጀግንነት ታሪኮች አሉት ሲሉ የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው ''የውጊያ ማርሽ ቀያሪዎቹ'' በሚል ርዕስ የተፃፈው መጽሐፍ ዛሬ በሐዋሳ ተመርቋል።   ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚሁ ወቅት፤ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የተፈጸሙ የጀግንነት ጀብዱዎች ተነግረው የማያልቁ ናቸው ብለዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝም በመጽሐፍ ተጽፈው የማያልቁ አኩሪ የጀግንነት ታሪኮች እንዳሉት ጠቅሰው፤ ይህን የጀግንነት ታሪክም ለቀጣዮቹ ጀግኖች በአግባቡ ሠንዶ ማስቀመጥ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሀገር ዳር ድንበርንና ሉዓላዊነትን ለማስከበር ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለ፣ ሀገርና ሕዝብ የሚኮሩበት ታሪክ የሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል። ''የውጊያ ማርሽ ቀያሪዎቹ'' መጽሐፍ በስድስት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን፤ የዕዙ ታሪኮችን በ526 ገጾቹ ያስቃኛል።   በዚህም መሠረት፤ የልዩ ዘመቻዎች ኃይል በኢትዮጵያ፣ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የአሁን ተጋድሎ ታሪክ፣ ድንበር ያልገደበው የጀግንነት ውሎ፣ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ቀደምት የተጋድሎ ታሪክ፣ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝና ሕብረተሰብ እንዲሁም የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የነገ ትልም በሚሉ ርዕሶች በየምዕራፉ ዝርዝር ሐሳቦችን ይዟል። መጽሐፉ ዕዙ ከተመሰረተበት ከ1953 ዓ.ም ጀምሮ እስከአሁን ያሉትን የ65 ዓመታት የተጋድሎ ታሪክ በፎቶ አስደግፎ መያዙም ተመላክቷል።
ማህበራዊ
በገጠር አካባቢ ያለው የመሰረተ ልማት ግንባታ አርሶአደሩን ተጠቃሚ አድርጓል
Feb 21, 2026 51
ሐረርጌ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የገጠሩን ማኅበረሰብ ጥያቄ ለመፍታት እያደረገ ባለው ጥረት የተሻለ ኑሮ እንድንመራ አስችሎናል ሲሉ በምዕራብ ሐረርጌ ዞን የቡርቃ ዲንቱ ወረዳ አርሶአደሮች ተናገሩ።   በወረዳው የሀሮ ጉራቻ ቀበሌ ነዋሪ አርሶአደር ጀማል አሕመድ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በአካባቢያቸው በተገነባው የፀሐይ ኃይል ማመንጫ የ24 ሠዓት መብራት እያገኙ ነው። የመብራትና ሌሎች አገልግሎቶችን ማግኝታቸው ኑሯቸውን ቀላል ማድረጉን አንስተዋል። አርሶ አደር አልቃድር ሼህ አሕመድም መንግሥት የገጠሩን ሕብረተሰብ ኑሮ ለመቀየር በመሥራቱ የተሻለ ኑሮ እንድንመራ እያደረገን ነው ብለዋል።   የቡርቃ ዲንቱ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ አሽም ቡሽራ እንዳሉት፤ በፌዴራል መንግሥት የተገነባው የፀሐይ ኃይል ማመንጫ፣ የጤናና የትምህርት ተቋማት የ24 ሠዓት ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ አስችሏል። እስካሁንም በሁለት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ2 ሺህ በላይ ነዋሪዎች አገልግሎቱን ያገኙ ሲሆን፤ በቀጣይ አራት ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የመስመር ዝርጋታ መከናወኑን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሀገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ዳይሬክተር ጥላሁን ብርሃኑ (ኢ/ር)፤ ከዋናው መስመር ርቀው የሚገኙ የገጠር አካባቢዎችን የፀሐይ ኃይል ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሠራ ነው ብለዋል። በቡርቃ ዲንቱ ወረዳ የተገነባው የፀሐይ ኃይል ማመንጫም ከ300 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትና ከ230 ኪሎ ዋት በላይ ኃይል ማመንጨት የሚችል መሆኑን አመልክተዋል።
የኮሪደር ልማቱ ለሥራ እና ለኑሮ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Feb 21, 2026 73
ቡታጅራ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፦ የኮሪደር ልማቱ ከተሞችን ከማስዋብ ባለፈ ለሥራ እና ለኑሮ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የሆሳዕና፣ የቡታጅራና የወልቂጤ ከተሞች ከንቲባዎች ተናገሩ። በሐዋሳ ከተማ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት ለነዋሪዎች በርካታ ዕድሎችን ይዞ መጥቷል የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ ሳሙኤል ሽጉጤ እንዳሉት፤ የኮሪደር ልማቱ የሆሳዕና ከተማን ለዕይታ ማራኪ፣ ለኑሮ ምቹ እና የኮንፈረንስ ቱሪዝም ተመራጭነቷን በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።   የቡታጀራ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አብዱ አሕመድ በበኩላቸው፤ ለኮሪደር ልማት ሥራው የሕብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ በመሆኑ ለስኬት መብቃቱን ገልጸዋል። የወንዝ ዳርቻዎችን በማስዋብ የመዝናኛ ስፍራ በማድረግ ተሸፍኖ የቆየውን የከተማዋን ውበት መግለጥ መቻሉንም ጠቅሰዋል።   የኮሪደር ልማቱ ወደ ኋላ ቀርቶ የነበረውን የወልቂጤ ከተማ እድገት ለማስጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ያረጋገጡት ደግሞ የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ ሙራድ ከድር ናቸው። ከተማዋ ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ የሚካሄድባትና ወደ ሌሎች አካባቢዎች የሚያልፉ ተጓዥች ማረፊያ በመሆኗ እንግዶች ተጨማሪ ጊዜን እንዲያሳልፉ የኮሪደር ልማቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል።   በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ስንታየሁ ወልደሚካኤል በበኩላቸው፤ በክልሉ በሰባት ከተሞች በኮሪደር ለማልማት ከታቀደው 165 ኪሎ ሜትር ውስጥ እስካሁን 47 ኪሎ ሜትር መጠናቀቁን አስታውቀዋል። የኮሪደር ልማቱ የከተሞቹን ንፅህናና ውበት ከማስጠበቅ ባለፈ፤ የአረንጓዴ ቦታዎች፣ የሕዝብ መዝናኛዎችና ማረፊያዎችን በመፍጠሩ ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ማድረጉንም ለኢዜአ አረጋግጠዋል።
በሐዋሳ ከተማ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት ለነዋሪዎች በርካታ ዕድሎችን ይዞ መጥቷል
Feb 21, 2026 60
ሐዋሳ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፦ በሐዋሳ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት ከውበት፣ ከስራ ዕድል ጋር በተያያዘ ለከተማዋ በርካታ ዕድሎችን ይዞ መምጣቱን ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ። ሶስተኛው ዙር የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት የተሻሉ ስራዎች የሚከናወኑበት መሆኑንም የከተማዋ ከንቲባ አስታውቀዋል። የበርካታ ቱሪስት መስህብ ስፍራዎች ባለቤት የሆነችው ሀዋሳ ከተማ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በስፋት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ የበለጠ አዲስ ውበትን አላብሷታል። በኮሪደር ልማቱ ማምሻቸውን በመዝናናት ላይ ከነበሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ኢዜአ ቆይታ ባደረገበት ወቅት ነዋሪዎቹ እንደገለፁት የኮሪደር ልማቱ ለከተማዋ በርካታ ዕድሎችን ይዞ መጥቷል። የሰርጋቸውን ፎቶ ለመነሳት ከአርቤጎና የመጡት አቶ ክፍሌ ዋቀዩ እና ወይዘሪት አንድነት አየለ፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋ በእጅጉ ውበትን እንድትጎናፀፍ አድርጓታል።   ለሰርጋችን ለምንነሳው የማስታወሻ ፎቶ ያማረ ገጽታ እንዲኖረው አድርጓል ነው ያሉት ሙሽሮቹ። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ ጥበቡ ደሳለኝ፤ የኮሪደር ልማቱ ጎልቶ ያልወጣውን የከተማዋን ፀጋ ባማረ መልኩ ጥቅም ላይ እንዲውል በማድረጉ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለመዝናናት እንደመጡ ይናገራሉ። በተለይም በምሽትም ሆነ በቀን ለመዝናኛነት ተመራጭ እንድትሆን ያደጉ የልማት ስራዎችን ለማየት መቻላቸውን ነው የገለጹት። የሀዋሳ ከተማዋ ነዋሪ የሆነው ወጣት አማኑኤል አለሙ፤ የኮሪደር ልማቱ ከውበት ባለፈ ለበርካታ ስራ አጥ ወጣቶች የስራ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን በተጨባጭ እየተመለከተ መሆኑን ነው የሚገልፀው። በኮሪደር ልማቱ የተገነቡት የመዝናኛ ስፍራዎች የስራ ባህልን ከመቀየር ባሻገር ለከተማዋ ተጨማሪ ገቢ ያስገኘ መሆኑንም ነው የሚናገረው። ሌላው አስተያየት ሰጪ ጃክ ፒተር በበኩሉ የኮሪደር ልማቱ በተለይ ለእግረኛም ሆነ ለተሽከርካሪና ምቹ ያልነበሩት መንገዶች ውበትን ተላብሰው አገልግሎት እንዲሰጡ አድርጓል ነው ያለው። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው፤ ሶስተኛውን ዙር የኮሪደር ልማት ስራ የሌሎች ከተሞችን ተሞክሮ በመቀመርና ነዋሪውን በማስተባበር በጥራትና በፍጥነት ለማካሔድ እየተሰራ ነው። በተለይ አመራሩ ከነዋሪው፣ ከባለሀብቱና ከመንግስት ሰራተኛው ጋር በመሆን ከተማዋን በጋራ ለመለወጥ እየሰሩ መሆኑንም ገልፀዋል።   በአሁኑ ወቅትም በሶስተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ፕሮግራም ከሀዋሳ ሀይቅ እስከ ሳውዝ ስታር አደባባይ የ3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር መንገድ እየተገነባ ነው ብለዋል። በሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ሲከናወን የነበረው ከ5 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሆነው የመንገድ ተግንባታ በተያዘው ሳምንት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆንም አረጋግጠዋል። የኢዜአ የዲጂታል ሚዲያ ገጾች https://linktr.ee/ENADigital
ኢትዮጵያ በሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ክትትልና ቁጥጥር ስኬታማ ተግባር አከናውናለች
Feb 21, 2026 53
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ጨምሮ በሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ክትትልና ቁጥጥር ስኬታማ ተግባር እያከናወነች መሆኗን የአፍሪካ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ገለፀ።   በማዕከሉ የወረርሽኝ መከላከል፣ ዝግጁነት እና ምላሽ ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ንጋሼ ንጎንጎ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስን ለመቆጣጠር ያደረገችው ርብርብ ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ለመቆጣጠር አስችሏል። ይህም ኢትዮጵያ ከፍተኛ ጉዳት ሳይደርስ በሽታን መቆጣጠር እንደሚቻል ትምህርት የሚወሰድባት ያደርጋታል ብለዋል። አክለውም ሀገሪቱ በጤና ኤክስቴንሽን መርሐ-ግብር አማካኝነት የበሽታዎች ልየታ ማከናወን የሚያስችል ጠንካራ የቅኝት ሥርዓት ዐቅም እንዳላት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።   የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትም ለሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝትና ቁጥጥር ትምህርት የሚሆን ልምድና የዝግጁነት ዐቅም መፍጠሩን ጠቅሰዋል። ማዕከሉ የኢትዮጵያ ጤና ዘርፍን ለማጠናከር በትብብር እየሠራ መሆኑንም ለኢዜአ አረጋግጠው፤ ለአብነትም የተለያየ የቴክኒክ እገዛ፣ የላቦራቶሪ ዐቅምን ማጠናከርና የግብዓት ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።   በአኅጉሪቱ የጤና ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥ ሀብትን ማሳደግ፣ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ማጎልበት፣ ውጤታማ አሠራርን ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ኢኮኖሚ
በመርሃ ግብሩ ታቅፈን በትጋት ሰርተን በመቆጠባችን ከተረጂነት ለመውጣት ችለናል-ተጠቃሚዎች
Feb 21, 2026 44
ድሬደዋ ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- በሴፍትኔት መርሃ ግብር ታቅፈው በትጋት ሰርተው በመቆጠባቸው ከተረጂነት ለመውጣት መቻላቸውን የድሬዳዋ የሚገኙ ሴት የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚዎች ተናገሩ። በከተሞች ተግባራዊ የተደረገው የልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጥሪት እንዲያፈሩ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። የሴፍትኔት ፕሮግራም በከተሞች የሚታየውን ሥራ አጥነትና ስር የሰደደ ድህነት በመቀነስ በኩልም የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የተለያዩ ተጠቃሚዎች ይገልፃሉ ። መርሃ ግብሩ በከተሞች ዜጎች የምግብ ዋስትናቸውን በሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የራሳቸው ገቢ እንዲኖራቸውና የቁጠባ ባህላቸውን እንዲያጎለብቱ የሚያግዝ ነው። በድሬዳዋ አስተዳደር የሴፍትኔት ተጠቃሚ የነበሩ ሴቶች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በሴፍትኔት መርሃ ግብሩ ጠንክረው በመስራትና ጥሪት በመቋጠር ወደ ሌሎች የልማት ስራዎች ለመሻገር መቻላቸውን ገልጸዋል።   በመርሃ ግብሩ ተሳትፎ ማድረጋቸው ተጠቃሚነታቸውን ለማጎልበት ማስቻሉን አመልክተው ከዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ በመውጣት የራሳቸውን መኖሪያ ቤት ለመገንባት እንደቻሉ በመጠቆም። በመርሃ ግብሩ በመታቀፍ ከተረጂነት ለመውጣት እንደቻሉ የተናገሩት ወይዘሮ እታገኝ በለጠ እና ወይዘሮ አበባ ኃይሌ እንዳሉት፤ በሴፍትኔት መርሃ ግብር ታቅፈን በትጋት በመስራታችን ከተረጂነት ለመውጣት ችለናል።   በተለይ ለሴቶች በንግድ ስራና በክህሎት ማሳደግ ላይ የተሰጠው ስልጠና አዋጪ በሆነ የገቢ ማግኛ ስራ ላይ በመሰማራት ከተረጂነት ለመውጣት ያስቻለና ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የመፍጠር እድልንም ፈጥሮልናል ብለዋል። መንግስት ተግባራዊ ባደረገው የሴፍቲኔት መርሃ ግብር በመሳተፍ ባገኘሁት ድጋፍና ስልጠና ራሴን ከመቻል ባለፈ የቁጠባ ሒሳብ ለመክፈትና ገንዘብ ለማስቀመጥ ችያለሁ ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ከዲጃ ኢብሮ ናቸው።   ከዚህ ባለፈም ልጆቻቸውንም በተገቢው መንገድ ለማስተማር መቻላቸውንም ነው የገለፁት።   በድሬዳዋ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅህፈት ቤት የከተማ ምግብ ዋስትና ዳይሬክተር አቶ አብዱልሰላም መድህኔ፤ መንግስት ተረጂነትን የሚጠየፍ ትውልድ ለማፍራት እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራት በውጤት እየታጀቡ መሆኑን ገልጸዋል። ከእነዚህ ሰው ተኮር የልማት እንቅስቃሴዎች ጎን ለጎን የሚደረጉ የገንዘብ ድጋፍና የሙያ ስልጠናዎች በድህነት ውስጥ የሚገኙ ሴቶችን ወደ አምራችነት እያሸጋገሩ መሆናቸውን በመግለፅ። በድሬዳዋ ከተማም በሴፍትኔት መርሃ ግብር ተጠቃሚ የሆኑ 340 የሚደርሱ ሴቶች በቆጠቡትና በተደረገላቸው የገንዘብ ድጋፍ በመታገዝ በተለያዩ የገቢ ማግኛ ስራዎች ላይ በመሰማራት ከተረጂነት ወደ አምራችነት መሸጋገራቸውን ነው የገለጹት።
የመንግስት የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው 
Feb 21, 2026 90
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የመንግስት የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ቢሮ ያዘጋጀው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያ ታምርት ኤግዚቢሽንና ባዛር የመክፈቻ መርኃ ግብር እየተካሄደ ነው። አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ውጤታማ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኙ ነው በመርኃ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እና ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን ተገኝተዋል።   ለአንድ ሳምንት የሚቆየው ኤግዚቢሽንና ባዛር "ኢትዮጵያ ታምርት፤ አዲስ አበባ ትበልፅግ" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተከፍቷል፡፡ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መንግሥት የአምራች ዘርፉን የሀገር ሉዓላዊነትና የጠንካራ መንግሥት መገለጫ አድርጎ ይመለከተዋል፡፡ አባቶቻችን የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ነጻነት ለማስከበር ዓድዋ ላይ ያስመዘገቡትን ጀብዱ መንግስት በኢኮኖሚው መስክ ለመድገም ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ለዚህ ስኬት ቁልፍ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ከማድረግ ጀምሮ የዘርፉን እድገት የሚያሳልጡ የተለያዩ ኢንሼቲቮችን ገቢራዊ አድርጓል ብለዋል፡፡   የአምራች ዘርፉ የጠንካራ ኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን በማንሳት፤ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ወሳኝ ርምጃዎች የአምራች ኢንዱስትሪው ሀገር አቀፍ የማምረት አቅም አጠቃቀም 66 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን አስታውቀዋል። በዚህም በኢትዮጵያ የሚመረቱ በርካታ ምርቶች ለታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች በግብዓትነት እያገለገሉ መሆኑን ገልጸው፤ አፈጻጸሙን ከዚህ በላይ ለማሳደግ መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዕድገት ከኢንዱስትሪ ዕድገት ጋር በእጅጉ የተሳሰረ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ከተማዋ የማምረቻ ማዕከል እንድትሆን በቅንጅት እንደሚሠራ ተናግረዋል፡፡ የምርቶችን ጥራት፣ መጠንና ብዝሃነት በማሳደግ በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ማድረግ፣ የፈጠራ ሥራዎችን በማበረታታት የማምረቻ መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ማጎልበት የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ የአምራች ዘርፉ ተዋንያን አጋርነታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቀርበዋል፡፡
አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ውጤታማ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኙ ነው
Feb 21, 2026 62
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ውጤታማ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኙ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ቢሮ ያዘጋጀው ከተማ አቀፍ የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ኤግዚቢሽንና ባዛር በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የመክፈቻ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡ የመንግስት የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው “ኢትዮጵያ ታምርት፤ አዲስ አበባ ትበልፅግ” በሚል መሪ ሀሳብ በተሰናዳው በዚህ መርኃግብር ላይ የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ለሀገር ሉዓላዊነት መከበርና ለብልፅግና መረጋገጥ መሰረታዊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ከንቲባዋ፤ በተለይም ከለውጡ ወዲህ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች አበረታች መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሁሉን አቀፍ የለውጥ ጉዞ የሚሰምረው ምርትና ምርታማነት ሲያድግ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ ይህንንም አሁን ላይ በተጨባጭ በውጤት እያየነው እንገኛለን ብለዋል፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የመዲናዋ ቀዳሚ የትኩረት መስክ መሆኑን ገልጸው፤ ለዘርፉ እድገት እንቅፋት የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት አስተዳደሩ በቁርጠኝነት ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል።   ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል ለኢንዱስትሪዎች የሚሆን የመስሪያ ቦታን ማመቻቸት፣ አምራቾች የገንዘብ አቅርቦት እንዲያገኙ ድጋፍ ማድረግ እንዲሁም የፈጠራ ባለቤቶችን በመደገፍ የዘርፉን ተግዳሮቶች መቅረፍ ለአብነት አንስተዋል፡፡ አስተዳደሩ ፈጣንና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ሚና የማሳደግ እቅድ ይዞ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ በመጪዎቹ ዓመታት ዘርፉ የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት እንዲሆን የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው፤ በከተማዋ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት በሙሉ ሁለንተናዊ ለውጥን ዓላማ ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በከተማዋ የሚገኙ አምራቾች የሀገር ውስጥ ግብዓት አጠቃቀማቸው 45 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፤ ይህም የዜጎችን የሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀም ባህል በከፍተኛ ደረጃ እየለወጠው መሆኑን ገልጸዋል።   በመዲናዋ 3 ሺህ 890 የሚደርሱ ኢንዱስትሪዎች እንደሚገኙና እነዚህም ለከተማዋ የኢኮኖሚ እድገት የላቀ ድርሻ እያበረከቱ መሆኑን አስረድተዋል። ይህ ንቅናቄ ምርትን ከማስተዋወቅ ባለፈ በአምራች ዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በመለየት ረገድ ችግር ፈቺ መፍትሔዎችን እያመጣ እንደሚገኝና ለዘርፉ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። አዲስ አበባ ሁሉም ኢንዱስትሪዎች በስፋት የሚያብቡባት ማዕከል እንድትሆን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። መንግስት የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነት ለማሳደግና የከተማዋን የኢኮኖሚ መዋቅር ስር ነቀል በሆነ መልኩ ለመቀየር የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ይህ ለአንድ ሳምንት የሚቆየው ኤግዚቢሽንና ባዛር የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለህዝብ ከማስተዋወቅ ባለፈ፣ በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ሰፊ የገበያ ትስስር እንደሚፈጥር ይጠበቃል።
የኮሪደር ልማቱ የሰሜን ሸዋ ዞን ከተሞችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድል ፈጥሯል
Feb 21, 2026 47
ደብረ ብርሃን ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡-የኮሪደር ልማቱ የሰሜን ሸዋ ዞን ከተሞችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድል መፍጠሩ ተመላከተ፡፡ በኢትዮጵያ በከተማና ገጠር እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የነዋሪዎችን የኑሮ ዘይቤ እያዘመነ ነው። የኮሪደር ልማቱ የከተሞችን ውበት ከመግለጥ ባለፈም ለዜጎች ዘመናዊ መሠረተ ልማትን ተደራሽ እያደረገ ይገኛል። በሰሜን ሸዋ ዞን የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ከተሞችን ለቱሪዝም፣ ለንግድና ኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጓቸው መሆኑም ተገልጿል። የሸዋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዘላለም መኮንን፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ከሌሎች አቻ ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ የሚያደርጋት ነው ብለዋል።   በከተማዋ ባለፈው ዓመት ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የመሸጋገሪያ ድልድይ፣ የጎርፍ መቀልበሻ ካናልና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ያካተተ አንድ ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ መሰራቱን አስታውሰዋል። በተያዘው ዓመትም ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የእግረኛ መንገድ፣ የመንገድ ዳር መብራትና ሌሎች ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል። የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን በማዘመን ሳቢና ውብ ከማድረጉ ባለፈ፣ በግንባታው ሂደት ለ500 ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል። የኮሪደር ልማቱ ዜጎች መንገድ፣ መብራትና ቴሌኮምን የመሳሰሉ ዘመናዊ መሰረተ ልማቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ ማድረጉንም አመልክተዋል።   የሰሜን ሸዋ ዞን ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ ብርቃብርቅ ተሾመ በበኩላቸው፤ በኮሪደር ልማት የሸዋ ሮቢትን ተሞክሮ በመውሰድ ልማቱን ወደ ሌሎች ከተሞች የማስፋፋት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ በለሚ፣ በአለም ከተማ፣ በአረርቲና በቡልጋ ከተሞች የ2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። እንደ አቶ ብርቃብርቅ ገለጻ፣ የኮሪደር ልማቱ በዞኑ የሚገኙ ታሪካዊ፣ ባህላዊና ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህቦችን ለጎብኚዎች ምቹ በማድረግ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን የሚያሳድግ ነው። የሸዋ ሮቢት ነዋሪዋ አሰገደች ኃይለስላሴና የዓለም ከተማ ነዋሪው አካሉ ደጀን፤ የኮሪደር ልማት ስራዎቹ የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ ለነዋሪዎች አዲስ የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል። ልማቱ ለኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን ተከትሎ ቀሪ ሥራዎችም በጥራትና በፍጥነት እንዲጠናቀቁ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ ነው
Feb 21, 2026 38
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢዲ ኮኔክት ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የ2026 የኢትዮ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ሳይንስ እና የትምህርት ፌስቲቫል ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።   ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ የመክፈቻ መርሐ ግብር ላይ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮችና ተማሪዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፤ በዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን ወጣቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለሀገሪቱ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ መሠረት መሆኑን ጠቁመው ፌስቲቫሉ ወጣቶች በትምህርት ልቀውና በሳይንስ መሪ መሆን እንዲችሉ ዓለም አቀፍ ልምድ ካላቸው ተቋማት ጋር ምህዳር እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ ከአጋር አካላት ጋር በመሆን የወጣቶችን የፈጠራ ስራ የሚያጎለብት "የሰመር ካምፕ" ለማዘጋጀት ማቀዱን ይፋ አድርገዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው፣ የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሰው ሀብት ልማት ላይ መስራት ቀዳሚ ተግባር ነው ብለዋል፡፡   ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ሥራዎች እንደ አማራጭ የሚታዩ ሳይሆን ለዘመናዊ ስልጣኔ መሰረት የሆኑ የልማት ምሰሶዎች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። የአፍሪካ ህብረት የጤና፣ ሰብአዊ መብቶች እና ማህበራዊ ልማት ኮሚሽነር አምባሳደር ሚንአታ ሳማቴ ሴሱማ፣ የወጣቶች ተሳትፎ ለአጀንዳ 2063 ስኬት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የዩኔስኮ የሰላም ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ጋይ ጆከን በበኩላቸው አፍሪካ ያላትን የወጣት ኃይል ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ እንደ ትልቅ ስትራቴጂካዊ ሀብት ሊወሰድ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢድ ኮኔክት ኢትዮጵያ መስራች ኢንጂነር ሳሙኤል ንጉሴ እንዳሉትም፤ ተቋማቸው ተማሪዎችን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሰራል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ የታደሙት ተማሪ ካይረን ግርማ እና ሲፈን ዮሃንስ በበኩላቸው፣ መድረኩ የትምህርት ዕድሎችን ለማግኘትና ዓለም አቀፍ እውቀትን ለመቅሰም ትልቅ በር እንደከፈተላቸው መስክረዋል። ፌስቲቫሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገውን የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ግቦች ከማሳካት አንጻር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና መሰረት የሚጥል ነው
Feb 21, 2026 55
ደሴ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡-ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥል መሆኑን የወሎ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። የአካል ጉዳተኞችን የፈጠራ አቅም በማጎልበት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ታዳጊዎች ለፈጠራና ለክህሎት እንዲጠቀሙበት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ይገባል ኢትዮጵያ የበለጸገ ኢኮኖሚ ባለቤት ለመሆን በምታደርገው ጥረት ውስጥ ቴክኖሎጂ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። የሀገሪቷን የ5 ዓመት የቴክኖሎጂ ልማት ጉዞ የሚመራበት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ወደ ሥራ ከገባ ሰነባብቷል። የስትራቴጂው ትግበራ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት በማፋጠን ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የወሎ ዩኒቨርስቲ ምሁራን ያነሳሉ። የዲጂታል ኢትዮጵያ ትግበራ በዋናነት የመንግስት አገልግሎቶችን በማዘመን፣ ብልሹ አሰራርን በመከላከልና ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል።   የወሎ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ሀዋ ወሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በየዘርፉ የተጀመሩ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራሮች ሥራን ከማቅለልና አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባለፈ ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ረገድ ተስፋ ሰጪ ውጤት እያስመዘገቡ ነው። ዩኒቨርሲቲው ይህንን ሀገራዊ ግብ ለማሳካት ቴክኖሎጂን የማስፋፋት፣ የማላመድና የጥናትና ምርምር ስራዎችን በትኩረት የማከናወን ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ጠቁመዋል። ተመራቂ ተማሪዎች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎትን እንዲታጠቁ በማድረግ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር የሥራ እድሎች ተጠቃሚ የሚሆኑበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነው ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የኢንፎርሜሽን ሲስተም መምህር ታደሰ ቢራራ በበኩላቸው፤ ሀገሪቱ ለዘርፉ የሰጠችው ትኩረት በ2030 የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል።   በቴሌ ብር፣ ሞባይል ባንኪንግ፣ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያና በ"ኢትዮ ኮደርስ" ስልጠናዎች የታየው ስኬት አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባለፈ ብልሹ አሰራርን መከላከልና ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባት እያስቻለ ነው ብለዋል። ግብርናን፣ ቱሪዝምንና ንግድን ከቴክኖሎጂ ጋር ማስተሳሰር መቻሉ ለሀገሪቷ ሁለንተናዊ እድገት መፋጠን መሰረት የሚጥል መሆኑንም ነው ያብራሩት። በገጠር አካባቢዎች የኢንተርኔትና የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት የቴክኖሎጂ ተደራሽነትን ማስፋትና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል። ወሎ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂን የተላመደ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራትና የሕብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
የአካል ጉዳተኞችን የፈጠራ አቅም በማጎልበት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል
Feb 21, 2026 48
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የአካል ጉዳተኞችን የፈጠራ አቅም በማጎልበት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተመላከተ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ "አካል ጉዳተኝነትን የሚያካትት ማህበረሰብ ለተሻለ ማህበራዊ ዕድገት" በሚል መሪ ሃሳብ 34ኛውን ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን በወላይታ ሶዶ ከተማ በተለያዩ ኹነቶች እያከበረ ይገኛል።   የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ካሰች ኤልያስ በወቅቱ እንዳሉት፤ የአካል ጉዳተኞች አካታችነትን በማጠናከር ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል። በአካል ጉዳተኞች ላይ የሚደርሱ አሉታዊ አመለካከቶችን በማስወገድ አቅማቸውን እንዲያወጡ የተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ውጤት ማሳየቱንም ጠቁመዋል። በዚህም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነታቸው እንዲያድግ እንዲሁም ድምፃቸው እንዲሰማ አርአያ ለሆኑ አካል ጉዳተኞች ዕውቅና የመስጠት እንዲሁም ተሞክሮአቸውን የማሸጋገር ተግባር ይጠናከራል ብለዋል።   በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቦጋለ ፈይሳ፤ አካል ጉዳተኞች አስፈላጊው ድጋፍ ከተደረገላቸው የፈጠራ አቅማቸውን በማውጣት ተጠቃሚ ሊሆኑ እንደሚችሉ ገልጸዋል።   በክልሉ የሚገኙ አካል ጉዳተኞች በርካታ ስራዎችን እየሰሩ መሆናቸውን በማንሳት እምቅ አቅማቸውን እንዲያወጡ ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ፤ አካል ጉዳተኞች ያላቸውን የፈጠራ እና የትምህርት ዕውቀት ለማውጣት ያለውን የአመለካከት ችግር ማረም ይገባል ብለዋል።   የለውጡ መንግስት ለአካል ጉዳተኞች የሰጠው ልዩ ትኩረት ተጠቃሚነታቸው እንዲያድግ ማድረጉንም ጠቁመዋል:: የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካል ጉዳተኞች ማህበራት ህብረት ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ደነቀ ዳጮ፤ በክልሉ የአካል ጉዳተኞችን ሰብዓዊ መብት በማስከበር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።   በመሆኑም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለውጥ አምጪ ፕሮግራሞችን በመቅረጽና ተሳትፏቸውን በማሳደግ አካል ጉዳተኞችን ሊደግፉ እንደሚገባም ገልጸዋል። በመድረኩ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የአካል ጉዳተኞች ማህበራት ተወካዮች ተገኝተዋል።
ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ታዳጊዎች ለፈጠራና ለክህሎት እንዲጠቀሙበት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ይገባል
Feb 21, 2026 66
አዳማ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የዲጂታል ቴክኖሎጂንና ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) ታዳጊዎች ለፈጠራና ለክህሎት ማጎልበቻ እንዲጠቀሙበት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚገባ ተገለጸ። ለታዳጊዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የበየነ-መረብና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀምን ተደራሽ ማድረግን ያለመ የባለድርሻ አካላት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል ።   ኢትዮጵያዊያን ታዳጊዎች ከዘመኑ ጋር አብረው እንዲራመዱና አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶችን እንዲያበረክቱ በዲጂታሉ አለም እውቀት እንዲያካብቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ በመድረኩ ተመላክቷል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኦሮሚያ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ፤ የወደፊቷ አገር የምትገነባው በሀገር ተረካቢዎች ፈጠራ እና ክህሎት መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም ታዳጊዎች ስልኮቻቸውንና ኮምፒውተሮቻቸውን ለጨዋታ ብቻ ሳይሆን፣ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና ለዲጂታል ፈጠራዎች እንዲያውሏቸው የማድረግ ሃላፊነት አለብን ብለዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂንና ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) ታዳጊዎች ለፈጠራና ለክህሎት ማጎልበቻ እንዲጠቀሙበት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚገባ አፅዕኖት ሰጥተዋል።   ለዚህም በተለይም ወላጆች፣ ትምህርት ቤቶችና የወጣቶች ማእከላት ትልቅ ሃላፊነት ያለባቸው መሆኑን ጠቅሰው ለነገዋ ብሩህ ኢትዮጵያ ዛሬ ልጆችና ታዳጊዎች ላይ እንስራ ሲሉ ተናግረዋል። የታዳጊዎችና ህፃናትን የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ጨምሮ በቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራም ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስገንዝበዋል። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በዲጂታል ትግበራና በሰው ሰራሽ አስተውሎት የትምህርትና የፈጠራ ማእከላትን በማስፋፋት በዘርፉ የተማረና የተመራመረ ትውልድ ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል።
ስፖርት
በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አዳማ ከተማ አሸንፈዋል 
Feb 21, 2026 23
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ20ኛ ሳምንት ሁለት ጨዋታዎች ማምሻውን ተደርገዋል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን 3 ለ 1 አሸንፏል። ዩጋንዳዊው ሳይመን ፒተር፣ ሁዘይፋ ሻፊ እና ሳምሶን ቹቹ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ታምራት እያሱ ለፋሲል ከነማ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ24 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ፋሲል ከነማ በ33 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሌላኛው መርሐ-ግብር አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አምበሉ ቢንያም አይተን በ61ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ አዳማ ከተማ በ31 ነጥብ አምስተኛ፣ የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ20 ነጥብ 16ኛ ደረጃን ይዘዋል። ቀን ላይ በተደረጉ የ20ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3፣ ባህርዳር ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፈዋል።
ወላይታ ድቻ እና ባህርዳር ከተማ በሊጉ ወደ አሸናፊነት የተመለሱበትን ድል አስመዘገቡ
Feb 21, 2026 52
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር መርሐ-ግብር ዛሬ በ20ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ተጀምሯል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ዛሬ ይጀመራል በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና እና አዲስ አበባ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወላይታ ድቻ ከ2 ለ 0 መመራት ተነስቶ መቻልን 4 ለ 3 አሸንፏል። ዮናታን ኤልያስ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ቴዎድሮስ ኃይለማርያም እና ካርሎስ ዳምጠው ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ለመቻል ቸርነት ጉግሳ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ በረከት ደስታ ቀሪዋን ጎል አስቆጥሯል። ከዘጠኝ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ወላይታ ድቻ በ19 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በውድድር ዓመቱ ሶስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በሊጉ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቻል በ30 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም።   በሌላ መርሐ-ግብር ባህርዳር ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ግርማ ዲሳሳ በ36ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ከአምስት ተከታታይ የአቻ ውጤቶች በኋላ ወደ ድል መንገድ የተመለሰው ባህርዳር ከተማ ደረጃውን ከዘጠነኛ ወደ ሰባተኛ ከፍ አድርጓል። በሊጉ አምስተኛ ድሉን አስመዝግቧል። በውድድር ዓመቱ ስምንተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሀዲያ ሆሳዕና በ24 ነጥብ ከነበረበት 10ኛ ደረጃ ወደ 11ኛ ዝቅ ብሏል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና እና አዲስ አበባ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል
Feb 21, 2026 50
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14 /2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር መርሐ-ግብር ዛሬ በ14ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ተጀምሯል። የኢትዮጵያ የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኟው ዙር ጅማሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ዛሬ ይጀመራል በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሲዳማ ቡና በዳሳሽ ሰውአገኝ ጎል ቦሌ ክፍለ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል። በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ድሉን ያስመዘገበው ሲዳማ ቡና በ18 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። በአንጻሩ በሊጉ ሶስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ቦሌ ክፍለ ከተማ በ23 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።   በሌላኛው መርሐ-ግብር አዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አማሩ አብተው እና አለሚ በዬቻ የማሸነፊያ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ሄለን እሸቱ ለልደታ ክፍለ ከተማ ብቸኛውን ግብ አስቆጥራለች።   በሊጉ ሁለተኛ ድሉን ያስመዘገበው አዲስ አበባ ከተማ በስምንት ነጥብ የመጨረሻውን 14ኛ ደረጃ ይዟል። በውድድር ዓመቱ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ልደታ ክፍለ ከተማ በበኩሉ በተመሳሳይ ስምንት ነጥብ በግብ ክፍያ በልጦ 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ የለሙ ተፋሰሶች በሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ ኢኮኖሚያዊ አቅማችንን አሳድገውልናል-ተጠቃሚዎች 
Feb 21, 2026 79
አርባ ምንጭ ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- በጋሞ ዞን የለሙ ተፋሰሶች ምርትና ምርታማነትን ከማረጋገጥ ባለፈ በሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ አኮኖሚያዊ አቅማቸውን ማሳደጉን በዞኑ የሚገኙ ተጠቃሚዎች ገለፁ። በምስራቅ ሸዋ ዞን ከ119 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ዕቀባ ሥራ እየተከናወነ ነው ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ወደ ትርፍ ምርት- የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት በዞኑ በበጀት ዓመቱ ወደ 160 ሺህ ሄክታር በሚጠጋ መሬት ላይ የተፋሰስ ልማት እየተከናወነ መሆኑም ተመላክቷል። ተጠቃሚዎቹ እንደገለፁት፤ በዞኑ የለሙ ተፋሰሶች ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ በሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ ኢኮኖሚያዊ አቅማችንን አሳድጎልናል ብለዋል። አርሶ አደር ሚሊዮን በየነ በዞኑ የቁጫ ወረዳ ነዋሪ ናቸው፤ በአካባቢያቸው ከዚህ ቀደም በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የተጎዳ መሬት ሲያገግም፣ የጠፋ ምንጭ ዳግም ሲፈልቅ እና የአካባቢው ስነ-ምህዳር ወደ ልምላሜ ሲቀየር በዓይናቸው ተመልክተዋል። አመቺ ባለመሆናቸው ለእርሻ ስራ ጥቅም ላይ ሳይውሉ የቆዩ የእርሻ ማሳዎች ጥቅም ላይ ውለው ወደ ምርታማነት ተቀይረው ሲመለከቱ ደግሞ እውን ሳይሆን ህልም መስሏቸውም ያውቃል። አሁን ላይ በተፋሰስ ልማት ስራው በለማው መሬት ላይም በእንስሳት እርባታና በንብ ማነብ ስራ ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ መሆን ጀምረዋል።   ለውጡንም በማየታቸው በዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ስራ ላይ ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆን ብቻም ሳይሆን ቤተሰባቸውንም በማስተባበር እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በአርባ ምንጭ ከተማ የ"ነህሚያ የእንስሳት እርባታ ማህበር" ሰብሳቢ ወጣት ህዝቅኤል ኦሎባ የማህበሩ አባላት የተፋሰስ ልማቱ በፈጠረላቸው ጸጋ ተነሳስተው ባለፈው ዓመት በሦስት ላሞች እና በሁለት ኮርማዎች ሥራ መጀመራቸውን አስታውሷል። በተፋሰሱ በለማው ቦታ ላይም መንግስት ባመቻቸላቸው ብድር ለእንስሳት መኖ በማምረት ተጠቃሚነታቸው እየጨመረ መሆኑንም ጠቅሷል። በአሁኑ ወቅት ከላሞቹ አምስት ጥጃዎችን ማግኘታቸውን የጠቀሰው ወጣቱ ለተለያዩ አካላት የወተት ምርት በማቅረብ የገቢ ምንጫቸው ማደጉን አስረድቷል፡፡ በአካባቢው የተከናወነው የተፋሰስ ልማት ጥሩ የስራ ዕድል ይዞልን መጥቷል ያለው ደግሞ በዞኑ ምዕራብ አባያ ወረዳ በአንኮበር ቀበሌ "የጦይሎ ንብ አንቢዎች ማህበር" ሰብሳቢ ወጣት አለማየሁ ቶጋ ነው። ማህበሩ በ2014 ዓ.ም እንደተመሰረተ የሚናገረው አለማየሁ በለማው ተፋሰስ ላይ በአንድ በኩል ንብ እያነቡ በሌላ በኩል የለማው ከባቢ እንዳይጎዳ ጥበቃ በማድረግ ላይ እንገኛለን ብሏል። መንግስት 30 ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን፣ አንድ የማር ማጣሪያ ማሽንና መስሪያ አልባሳት እንዳበረከተላቸው ገልጾ አስፈላጊው የሙያ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም አልሸሸገም። ''በዓመት ከ3 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ ማር እየሸጥን ራሳችንን ከመቻል ባለፈም ቤተሰቦቻችንን እያገዝን እንገኛለን'' ብሏል።   የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ወርቅነህ ካልሳ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ የተፋሰስ ልማት በተለያየ መልክ የዞኑን ህዝብ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል። የተጎዳ መሬትን እንዲያገግም በማድረግ ብሎም ስነ-ምህዳርን በማስተካከል ምርትና ምርታማነት እንዲረጋገጥ በማስቻል የአርሶ አደሮችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል። ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጋር በተያያዘ የነዋሪዎች ግንዛቤ እየሰፋ በመምጣቱ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ጋር ተዳምሮ ምርት በስፋት እየተመረተ ይገኛል ብለዋል። በያዝነው በጀት ዓመትም በ336 ንዑስ ተፋሰሶች 160 ሺህ ሄክታር በሚጠጋ መሬት ላይ የተፋሰስ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውንም አቶ ወርቅነህ ገልጸዋል።
ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ወደ ትርፍ ምርት- የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት
Feb 21, 2026 52
ደሴና ደብረ ማርቆስ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ወደ ትርፍ ምርት-የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት በምስራቅ ሸዋ ዞን ከ119 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ዕቀባ ሥራ እየተከናወነ ነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአፈር ለምነትን በማሻሻል ምርታማነትን እያሳደገ መሆኑን አርሶ አደሮች ይመሰክራሉ። ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተከለቻቸው በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች የአፈር ለምነትን በመመለስና የተፈጥሮ ሀብትን በመጠበቅ ረገድ ተጨባጭ ውጤት ማምጣታቸውን ከአርሶ አደሩ ባለፈ የተለያያዩ አለም አቀፍ ተቋማት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። በመርሃ-ግብሩ የተከናወኑ የአፈርና ውሃ እቀባ ሥራዎች ቀደም ሲል ተራቁቶ የነበረን መሬት እንዲያገግም አድርገዋል።   ደርቀው የነበሩ ምንጮች እንዲፈልቁና የወንዞች የውሃ መጠን እንዲጨምር በማድረግም ለመስኖ ልማት ምቹ ሁኔታን ፈጥረዋል። ይህም በምርታማነት ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣ ሲሆን፣ በአንዳንድ አካባቢዎች በግማሽ ሄክታር መሬት ላይ ይገኝ የነበረውን 7 ኩንታል ምርት ወደ 20 ኩንታል አሳድጓል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የምስራቅ ጎጃምና የደቡብ ወሎ ዞን አርሶ አደሮችም በአረንጓዴ አሻራ የታገዘው የአፈርና ውሃ እቀባ ሥራ ምርታማነታቸውን በእጥፍ ማሳደጉን ይናገራሉ።   በምስራቅ ጎጃም ዞን የደጀን ወረዳ የሽንቡሪ ቀበሌ አርሶ አደር በቃሉ ፈቃድ እንደሚሉት፣ ቀደም ሲል በእርሻ ማሳቸው ላይ ይገጥማቸው የነበረው የአፈር መሸርሸር ለምርታማነት መቀነስ ዋነኛ ምክንያት ነበር። ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ያከናወኑት የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ የእርሻ ማሳቸውን ለምነት በከፍተኛ ደረጃ እንዲጨምር አድርጓል። ከ10 ዓመት በፊት በግማሽ ሄክታር መሬት ላይ ያገኙት የነበረው ምርት ከ7 ኩንታል በታች እንደነበር አስታውሰው፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በመታገዝ የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ በመስራታቸው አሁን ላይ ከ20 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚያገኙ አመልክተዋል። ይህ ውጤት በዘንድሮው በጋ እየተካሄደ በሚገኘው የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ ላይ ያለማንም ቀስቃሽ በቁርጠኝነት ለመሳተፍ መነሳሳትን እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል። የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራው ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ለውሃ ሀብት መጨመር ምክንያት ሆኗል። በምስራቅ ጎጃም ዞን የጎዛምን ወረዳ አርሶ አደር በእድሉ ጫኔ በበኩላቸው፣ ባለፉት ዓመታት ባከናወኗቸው የተፈጥሩ ሃብት ጥበቃ ሥራዎች የከርሰ ምድር ውሃ መጨመሩንና ደርቀው የነበሩ ምንጮች መፍለቃቸውን አመልክተዋል። ይህም ለመስኖ ልማት ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስራ ላይ በመሰማራት ተጨማሪ ገቢ እንዳገኝ አድርጓል ብለዋል።   በደቡብ ወሎ ዞን አርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ተመሳሳይ ስኬቶች እየተመዘገቡ ነው። አርሶ አደር ሱለይማን መሀመድ እና ያስን መሀመድ እንደተናገሩት፣ በአረንጓዴ አሻራ የተሰሩ እርከኖችና ክትሮች የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረጋቸው በየሄክታሩ ከ2 እስከ 3 ኩንታል የምርት ጭማሪ አግኝተዋል።   የወል መሬቶችን በማልማትም በቆላ ፍራፍሬና በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ለአካባቢው ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል መፈጠሩን አስረድተዋል። የምስራቅ ጎጃም ዞን የግብርና መምሪያ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ ንጉሴ ሽመልስ እንደገለጹት፣ በዘንድሮው በጋ ከአንድ ሺህ በላይ ተፋሰሶች ላይ 84 ሺህ ሄክታር መሬትን የሚሸፍን የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ ለማከናወን ታቅዶ እስካሁን ከ50 በመቶ በላይ ተከናውኗል።   በተመሳሳይም የደቡብ ወሎ ዞን የግብርና መምሪያ ኃላፊ አህመድ ጋሎ፣ በዞኑ በ58 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ስራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱንና እስካሁን ከ33 ሺህ ሄክታር በላይ መከናወኑን ገልጸዋል።   አርሶ አደሩ በዘርፉ እያገኘ ያለው ተጨባጭ ጥቅም ለስራው ስኬታማነት ትልቁን ድርሻ እየተወጣ መሆኑንም አመልክተዋል።
በምስራቅ ሸዋ ዞን ከ119 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ዕቀባ ሥራ እየተከናወነ ነው 
Feb 21, 2026 62
አዳማ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን በበጋ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ከ119 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ዕቀባ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ እንዳሉት፤ የዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ሥራ ከጥር አጋማሽ ጀምሮ በህዝብ ተሳትፎ በሁሉም መዋቅሮች እየተካሄደ ይገኛል። ልማቱ እየተከናወነ ያለው በዞኑ በ11 ወረዳዎች ከ119 ሺህ ሄክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ በሚገኙ ተፋሰሶች ላይ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም የተለያዩ የአፈርና የድንጋይ እርከኖች፣ የእርጥበት ማቆያዎች፣ የክትር ሥራዎች፣ የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮች ስራዎች በፍጥነት እየተከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።   እንዲሁም በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግር ለጉዳት የተጋለጠ መሬት ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ የመከለል ሥራም ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል። የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራውን ለማቀላጠፍ በየደረጃው የሚገኙ የግብርና ባለሙያዎች የቅርብ ድጋፍና ክትትል እያደረጉ መሆኑን ተናግረው ልማቱ በሚከናወንባቸው ቦታዎችም የችግኝ ጉድጓድ ቁፋሮ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት በተሰራው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት አካባቢው ልምላሜና ነፋሻማ አየር መላበሱን ጠቅሰው የአፈር መሸርሸር ቀንሶ እርጥበት በመጨመሩ ምርትና ምርታማነት ማደጉን በማሳያነት ጠቅሰዋል። እንዲሁም የአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች የግብርናና የእንስሳት ምርትና ምርታማነት መጨመሩን፣ የከርሰ ምድር ውሃ መጎልበቱንና ለመስኖና ለጓሮ አትክልት ልማት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም አቶ አብነት አስረድተዋል። በዞኑ የቦሰት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጉተማ ቢፍቱ በወረዳው እየተካሄደ ባለው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ ላይ በርካታ አርሶ አደሮች፣ የወጣቶች እና የሴቶች አደረጃጀቶች በንቃት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።   ‎በበጋው የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ የማሳና የጋራ ላይ እርከን፣ የውሃ ማፋሰሻና መቀልበሻ ቦዮች እንዲሁም የተለያዩ የውሃ ማስረጊያ ስትራክቸሮች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። ‎ይህም የአፈር ለምነት እንዲሻሻልና ምርታማነት እንዲጨምር ከማድረግ ባለፈ በተፋሰሶቹ በዘላቂነት የእንስሳት መኖ ለማግኘት እና ልቅ ግጦሽን ለመከላከል ምቹ መደላድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል። ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የአካባቢውን ሥነ ምህዳር ከመለወጡም በተጨማሪ ከሰውና እንስሳ በተከለሉ መሬቶች ላይ አርሶ አደሩ የእንስሳት መኖን እያገኘ መሆኑን ጠቁመዋል።
ነፋሻማው የጎዴ ፓርክ በወጣቶች ተመራጭ የመዝናኛ ሥፍራ ሆኗል
Feb 19, 2026 94
ጎዴ፤ የካቲት 12/2018 (ኢዜአ) ፡-ነፋሻማው የጎዴ ፓርክ በወጣቶች ተመራጭ የመዝናኛ ሥፍራ ሆኗል። በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የመሰረተ ልማት፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል። የከተማዋን ውበት የሚገልጡና የክልሉን እድገት የሚያፋጥኑ የወጣቶች መዝናኛና መናፈሻ ስፍራዎች መገንባታቸው ደግሞ የአካባቢውን ገጽታ ከመቀየር አኳያ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው። በሞቃታማዋ ጎዴ ከተማ የተገነባው የክፍለ ዘመን መዝናኛ ፓርክ የዚሁ አካል ሲሆን በፓርኩ የሚገኙ እጽዋት አካባቢውን ነፋሻማ በማድረግ ለወጣቶች አማራጭና ተመራጭ መዝናኛ ሥፍራ ሆኗል።   አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ወጣቶች ፓርኩ ውብና አረንጓዴ በመሆኑ ሞቃታማውን የአካበቢውን አየር ጸባይ ነፋሻማና ምቹ አድርጎታል ይላሉ። የከተማዋ ወጣቶች ለመዝናናትም ሆነ ለንባብ የሚመርጡት ቦታ መሆኑንም ተናግረዋል። ወጣት ሀምዛ አብዱልዋሃብ እንደሚለው ፓርኩ ወጣቶች ጊዜያቸውን በአልባሌ ስፍራ እንዳያሳልፉ አማራጭ መዝናኛ ሆኗል። ወደ ፓርኩ በተደጋጋሚ በመምጣት አንደሚያነብና እንደሚዝናናም ገልጿል። ለተለያዩ ዝግጅቶች ፓርኩን ተመራጭ መዳረሻ እንደሚያደርግ የገለጸው ደግሞ ወጣት ሳዳም ሁሴን ነው። ፓርኩ ከአካባቢው ወጣቶች ባለፈ ወደ ጎዴ ለሚመጡ እንግዶች ተመራጭ የመዝናኛ ቦታ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት ዴቃ መሀመድ በበኩሏ የፓርኩ መገንባት ውብና አረንጓዴ አካባቢ በመፍጠር በነፋሻማ አየር ጊዜዋን አንድታሳልፍ ዕድል መፍጠሩን ገልጻለች።   የጎዴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱላሂ አሊ፣ ከተማዋን አረንጓዴና ዉብ የማድረግ ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው ብለዋል። ፓርኩ ለወጣቶች አማራጭ የመዝናኛ ቦታ ከመሆን ባለፈ ለአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና የፈጠረውን የንግድ ትስስር ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት ወሳኝ ነው
Feb 21, 2026 64
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን የንግድ ትስስር ዕድል በአግባቡ ለመጠቀም በመንግሥታትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለ አጋርነትን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ።   የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የስምምነቱ ትግበራ የንግድ መሰናክሎችን በማስቀረት የሀገራትን የንግድ ልውውጥ ለማሳለጥ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተ ነው። እስካሁን 50 ሀገራት ፈርመው ያጸደቁት ይህ የንግድ ቀጣና፤ በዲጂታል የኢኮኖሚ ዕድገት የፋይናንስ ቴክኖሎጂን በማስፋት የአኅጉሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በማዘመንና የገንዘብ ዝውውርን በማቀላጠፍ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት የአሰራር ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተዳራሽ ለማድረግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ዘርግቷል የኢትዮጵያ ቱሪዝም አዲሱ ገጽታ፤ ከአማራጭ ማጣት ወደ መዳረሻዎች ብዛት በኢትዮጵያ ለግል ዘርፉ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ ኢኮኖሚው እየተነቃቃ ነው የአፍሪካን የተፈጥሮ ሃብትም በተሻለ የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነት በማልማት የመሰረተ ልማት፣ የዋጋ ግሽበትና የንግድ መሰናክሎችን ለመቀነስ አይነተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም አስረድተዋል።   በዚህም አባል ሀገራት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን በማፋጠን የእርስበርስ የንግድ ልውውጥን ማሳለጥ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን ዕድል ለመጠቀም የግሉ ዘርፍና የአባል ሀገራት መንግሥታት የእርስ በርስ የንግድ ልውውጥን ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሰረትም የአባል ሀገራት ኢንቨስትመንትን የሚያነቃቃ የኢንቨስትመንት ጥበቃ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስረድተዋል። የስምምነቱ የኢንቨስትመንት ጥበቃም የአፍሪካን በመተማመን ላይ የተመሰረተ የእርስበርስ ንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ለማጎልበት የሚያስችል መሆኑን አስታውቀዋል።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና የቱርክዬ ታሪካዊ አጋርነት 
Feb 16, 2026 303
የኢትዮጵያ እና ቱርኪዬ ግንኙነት ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የአፍሪካ ጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ ኦቶማን ኢምፓየርን ጨምሮ በታሪክ ከመካከለኛው ምስራቅ እና አውሮፓ ጋር ታሪካዊ ግንኙነት ነበራት። ኦቶማን ኢምፓየር ለዘመናዊቷ ቱርክዬ መሰረት ጥሎ አልፏል። በ20ኛ ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት በዲፕሎማሲ እና ንግድ ልውውጥ ላይ የተመረኮዘ ነው። ቱርክዬ አፍሪካን እንደ ስትራቴጂካዊ አጋር የምትቆጥር ሲሆን አፍሪካ ህብረትን ጨምሮ ቁልፍ አህጉራዊ ተቋማት የሚገኙባት እና የአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ የዚህ ትብብር አካል ናት። ኢትዮጵያ እና ቱርክዬ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ 1896 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የመጀመሪያ የኦቶማን-ቱርክዬ ቆንስላ ጽህፈት ቤት እ.አ.አ በ1912 በሐረር ከተማ ተከፍቷል። ቱርክዬ ከሰሃራ በታች የመጀመሪያውን ኤምባሲ የከፈተችው በኢትዮጵያ ሲሆን ወቅቱም እ.አ.አ በ1926 ነበር። ኢትዮጵያ በቱርክዬ ኤምባሲዋን የከፈተችው እ.አ.አ በ1933 ነው። ያለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያ እና የቱርክዬ ግንኙነት ከፍተኛ እድገት ያሳየበት ነው። ኢኮኖሚ የሁለቱ ሀገራት አጋርነት ምሰሶ እንደሆነ ይጠቀሳል። የቱርክዬ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጨርቃ ጨርቅ፣ በግንባታ እና በግብርና ማቀነባበሪያ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ተሰማርተው ይገኛሉ። ቱርክዬ በኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ካላቸው ሀገራት መካከል በዋናነት ትጠቀሳለች። የሀገራቱ የንግድ ግንኙነትም እየዳበረ መጥቷል። ከኢኮኖሚ ባሻገር ፖለቲካ፣ ደህንነት፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንዱስትሪ እና ባህል ሌሎች የትብብር መስኮች ናቸው። ባለፉት 10 ዓመታት በሁለቱ ሀገራት መካከል የከፍተኛ ባለስልጣናት የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። የቱርክዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ጉብኝቱ የሀገራቱን የሁለትዮሽ ትስስር ማጠናከርን ያለመ ነው። እ.አ.አ በ2017 የቀድሞ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በቱርክዬ ጉብኝት በማድረግ ኢትዮጵያን በመወከል በቱርክዬ-አፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ላይ ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እ.አ.አ በ2021 በቱርክዬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ ሀገራቱ በተለያዩ ዘርፎች የትብብር ስምምነቶች መፈራረማቸው ይታወሳል። ውሃ፣ ወታደራዊ ትብብር እና ፋይናንስ ከስምምነቶቹ ትኩረቶች መካከልም ይገኙበታል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የተደረገው ኢትዮጵያና ቱርክዬ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበት 125ኛ ዓመት ላይ መሆኑ ልዩ ትርጉም የሚሰጠው ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት የተፈረሙት ስምምነቶች የግንኙነቱን መጠናከር እንደሚያመለክቱ ገልጸዋል። ለኢትዮጵያ የልማት እና መረጋጋት ጉዞ ቱርክዬ የምታደርገውን ድጋፍም አድንቀዋል። የቱርክዬ መንግስት እና ህዝብ ያደረገልንን የወሳኝ ጊዜ ትብብር ሀገራችን ኢትዮጵያ መቼም አትረሳውም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ በነበራቸው ቆይታ። የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እ.ኤ.አ በ2021 በቱርክዬ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ አዲስ የተገነባውን የኢትዮጵያ ኤምባሲም መርቀዋል። የቱርክዬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እ.አ.አ በ2024 ኢትዮጵያን በመጎብኘት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የከፍተኛ ባለስልጣናቱ ጉብኝት የሀገራቱን የግንኙነት መጠናከር የበለጠ የሚያጎለብቱም ናቸው። ኢንዱስትሪ እና ማኑፋክቸሪንግ፣ መሰረተ ልማት፣ የንግድ ብዝሃነትን ማስፋት፣ መከላከያ እና ደህንነት፣ ቱሪዝም እና ባህል ሀገራቱ ትብብራቸውን ሊያሰፉባቸው እየሰሩባቸው ከሚገኙ መስኮች መካከል ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ እና የቱርክዬ አጋርነት በጋራ ፍላጎቶች፣ ተራማጅ በሆኑ ሀሳቦች፣ በጋራ ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እና እየተለወጡ ያሉ የዓለም እውነታዎችን ባማከለ ሁኔታ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። በልማት ጎዳና ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ እና ቱርክዬ ከአፍሪካ ጋር ያላት ትስስር የሁለቱን ሀገራት ስትራቴጂካዊ ትብብር የበለጠ ጥልቀት የሚሰጥ ነው። ሁለቱ ሀገራት በፍጥነት እየተለዋወጠ በሚገኘው ቀጣናዊ እና የዓለም ምህዳር ውስጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ለማጠናከር እየሰሩም ይገኛሉ።
የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋርነታቸውን ለማደስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለጹ
Feb 16, 2026 135
አዲስ አበባ፤ የካቲት 9/2018(ኢዜአ):- የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የአህጉሪቱን የፋይናንስ መዋቅር ማጠናከርን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት በአዲስ መልክ ለማደስ እንደሚሰሩ አስታወቁ። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሂዷል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከጉባኤው ጎን ለጎን ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ(ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ባንኩ ለአፍሪካ ቁልፍ የትኩረት መስኮች እያደረገ ያለውን ጠንካራ ድጋፍ ያደነቁ ሲሆን ለአፍሪካ ልማት ፈንድ 11 ቢሊን ዶላር ተጨማሪ ገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን መልካም የሚባል እርምጃ መሆኑን አመልክተዋል። ሊቀመንበሩ እና የባንኩ ፕሬዝዳንት ከእዳ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የደህንነት ፈተናዎች ባለፈ የፋይናንስ አቅርቦት የአፍሪካ አበይት ፈተና መሆኑን በምክክራቸው ወቅት ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች የፕሮጀክት ዝግጅት ትብብርን ለማጠናከር፣ የአንድ ትሪሊን የአሜሪካን ዶላር የአፍሪካ ካፒታል ማሰባሰብ፣ የአፍሪካ የብድር ምዘና ኤጀንሲን ማጎልበትና ጠንካራ የአፍሪካ የፋይናንስ ስርዓት መገንባት ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በውይይቱ የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋርነታቸውን በአዲስ መልክ ለማደስ ተሠማመተዋለ። በዓመት ሁለት ጊዜ ለመወያያት እና በአፍሪካ ፋይናንስ ላይ የከፍተኛ ደረጃ ምክክር ለማካሄድ እቅድ መያዛቸውንም ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዘጠነኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል
Feb 16, 2026 183
አዲስ አበባ፤ የካቲት 9/2018 (ኢዜአ):- ዘጠነኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ከዛሬ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል። የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሴኤ) ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ሁነቱን አዘጋጅተውታል። “የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ በፋይናንስ መደገፍ፤ ሥራ እና ኢኖቬሽን ለዘላቂ ትራንስፎርሜሽን” የፎረሙ መሪ ሐሳብ ነው። የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም በአፍሪካ የልማት እና የኢኮኖሚ እድገት ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን በማድረግ በየዓመቱ የሚካሄድ ከፍተኛ አኅጉራዊ የምክክር መድረክ መሆኑን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። አኅጉራዊው መድረክ የአፍሪካ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያንና የልማት አጋሮችን በአንድ መድረክ ያገናኛል። ፎረሙ አጋርነትና የኢንቨስትመንት መጠንን ማሳደግ በተለይም የመንግሥት እና የግል የተቀናጀ የፋይናንስ አቅርቦትን ጨምሮ የተለያዩ የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይወያያል። የሥራ ዕድል፣ ምቹ የኢኖቬሽን ሥነ-ምኅዳር እና የአፍሪካን የፈጠራ ዐቅም አሟጦ መጠቀም በፎረሙ ላይ ምክክር ከሚካሄድባቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። በተለይም የዲጂታል ኢንዱስትሪዎች፣ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም እየሰፋ ያለው የአፍሪካ የፈጠራ ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቶታል። በፎረሙ የተለያዩ ኢኒሼቲቮችና ማዕቀፎች ይተዋወቃሉ። የወጣቶችን የኢኖቬሽን ሥራ ከፋይናንስ አቅርቦት ጋር የሚያስተሣሥር የአፍሪካ የወጣቶች አይበገሬነትና ትራንስፎርሜሽን ማዕቀፍ ይፋ ይሆናል። በኢሲኤ የበለጸገውና የመንግሥት እና የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ ቃል ኪዳኖችን ትግበራ የሚከታተልና የሚቆጣጠር ሥርዓትም በፎረሙ ይፋ ሆኖ ወደ ትግበራ ይገባል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው ሁነት ላይ የአፍሪካ ሀገራት የመሪዎች የምክክር መድረኮችና የባለሙያዎች ውይይቶች ይደረጋሉ። አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችና የፈጠራ ባለሙያዎችን ከባለሀብቶች እና ፋይናንስ አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኝ ዐውደ-ርዕይም ይካሄዳል። ሁነቶቹ ቃል ኪዳኖችን ወደ ተጨበጡ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር አስተዋጽዖ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል። የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም በዘላቂ ልማት ግቦችና በአጀንዳ 2063 የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ ስትራቴጂካዊ ሚናውን እየተወጣ እንደሚገኝም በመረጃው ተመላክቷል። የኢዜአ የዲጂታል ሚዲያ ገጾች https://linktr.ee/ENADigitalክቷል።
ሐተታዎች
   የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 134
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን።   የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው።   የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል።   የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት።   የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 586
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ።   በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 927
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 853
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 986
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 945
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 1496
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3809
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3467
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2297
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8089
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6575
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60302
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54263
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34858
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32423
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27640
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26656
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26175
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25931
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60302
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54263
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34858
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32423
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ ዐሻራ ከዓድዋ - እስከ አፍሪካ ኅብረት
Feb 14, 2026 241
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የፖለቲካ፣ የታሪክ እና ዲፕሎማሲ ምኅዳር ውስጥ ልዩ ስፍራ እና ተጽዕኖ ያላት ሀገር ናት። የጥንታዊ ሥልጣኔዎች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ፤ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ የአፍሪካ ሀገር ከመሆኗ ባሻገር ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ መስፋፋት ትልቅ ሚና ተጫውታለች። ይህንም ታሪክ ይዘክራል። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ዛሬ ይጀመራል አይበገሬነት፣ ሉዓላዊነት እና የፓን አፍሪካ መንፈስ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ካሳረፈቻቸው ዐሻራዎች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። በዘመናዊው ዓለምም በአፍሪካ አጀንዳዎች ላይ ወሳኝ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነጻነት እና ማንነት ተምሳሌት ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1896 በዓድዋ ጦርነት በጣሊያን ኃይሎች ላይ የተቀዳጀችው ድል በአፍሪካ እና በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ የሚሰጠው ነው።   አብዛኛው የአፍሪካ አኅጉር በቅኝ ግዛት ውስጥ በነበረበት ወቅት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ድል ሉዓላዊነቷን ከማስጠበቅ ባለፈ በአፍሪካ እና በአፍሪካ ዳያስፖራ የነጻነት ትግሎች እንዲቀጣጠሉ አድርጓል። በተለይም ከ20ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ ለነበሩ እንቅስቃሴዎች ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ይህ ታሪካዊ ዐሻራ ኢትዮጵያን የጥቁሮች ኩራት፣ ትግል እና ራስን የመቻል ምልክት እንድትሆን አስችሏታል። የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና አዲስ አበባ የአፍሪካ ኅብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ ኢትዮጵያ የአኅጉሪቷ የዲፕሎማሲ ማዕከል ሆና እንድትቀጥል አስችሏል። እ.አ.አ በ1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ኅብረት) ታሪካዊ ምሥረታ የተካሄደው በኢትዮጵያ ነው። ኢትዮጵያ ከድርጅቱ መሥራች ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ይህም የአፍሪካ የጋራ የፖለቲካ ድምጽ እንድትሆን ምክንያት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሴኤ) እና ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ተቋማት የሚገኙባት ኢትዮጵያ፤ በዲፕሎማሲው ምክክር እና ውሳኔ ሰጪነት ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የበለጠ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ድምጽ ኢትዮጵያ በቅኝ አለመገዛቷ ለፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ ሥር መስደድ ወሳኝ ነው። በፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ለአፍሪካ አንድነት እና የጋራ ምላሽ አጥብቃ ስትሞግትም ቆይታለች። በአፍሪካ ኅብረት እና በተለያዩ መድረኮች ኢትዮጵያ የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን መፈታት አለባቸው የሚለውን እሳቤ ለማስረጽ አበክራ እየሠራች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተኮር መፍትሔዎች ከቃላት ባለፈ በአኅጉራዊ የትሥሥር አጀንዳዎች፣ ሰላም እና ደኅንነት ማዕቀፎች እንዲሁም የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ፈተናዎች እንዲፈቱ ድጋፏን በመስጠት ቁርጠኝነቷን አሳይታለች። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነትንም በፍጥነት አጽድቃ ወደ ሥራ ማስገባቷ የዚሁ አንድ ማሳያ ነው። ሰላም ማስከበር እና ቀጣናዊ መረጋጋት ኢትዮጵያ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ስትራቴጂካዊ ሚና እየተወጣች ነው። በዚህም መሠረት ለተባበሩት መንግሥታት እና የአፍሪካ ኅብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማድረግ ከአፍሪካ ሀገራት ቀዳሚውን ድርሻ ትይዛለች።   ሶማሊያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ ግጭት ባለባቸው የአፍሪካ ሀገራት ወታደሮቿን በመላክ ለሰላም እና ደኅንነት ያላትን ሚና በተግባር ገልጣ አሳይታለች። የተባበሩት መንግሥታትም ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር እየተወጣች ላለው ሚና ምሥጋናውን ማቅረቡ ይታወቃል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሀገራት ያሉ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የተወጣችው የእርቅ እና የዲፕሎማሲ ሚናም ተጠቃሽ ነው።   የኢኮኖሚ እድገት እና ቀጣናዊ ትሥሥር ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል በዋናነት ትጠቀሳለች። በ2017 ዓ.ም ማብቂያ የተመረቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በግንባታ ላይ የሚገኘው ኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከግዙፍ መሠረተ ልማትነታቸው ባለፈ ቀጣናዊ ትሥሥር በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሚና አላቸው። ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢነርጂ የስኅበት ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል። ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት የምትሸጠው ኢነርጂ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን የሚያሳልጥ ነው። የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መንገድን ጨምሮ የመንገድ መሠረተ ልማቶች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኢትዮጵያን የቀጣናዊ ትሥሥር ማዕከል እንድትሆን እያደረጓት ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት እየተከናወነ ያለው አረንጓዴ ዐሻራም፤ ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ትብብር እና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተምሳሌት ማድረግ ችሏል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ አጀንዳ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ትገኛለች። የባህል እና የሥልጣኔ አስተዋጽዖ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ታሪክ፣ ቱባ ባህል እና ብዝኃነት መገለጫዋ ናቸው። የቋንቋ ብዝኃነት በአፍሪካ ውስጥ ገራገር የዲፕሎማሲ ኃይል (Soft Power) እንዲኖራት አስተዋጽዖ አድርጓል። የኢትዮጵያ የሀገርነት ታሪክ እና የሥልጣኔ ትርክት አፍሪካ ያሏትን ጥልቅ የታሪክ ሥሮች ይበልጥ አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የኢትዮጵያ ብዝኃ ማንነቶች፣ ሀገር በቀል ዕውቀቶች እና አስደማሚ የሥነ-ሕንጻ ሥራዎች በአፍሪካ ባህል እና ሥልጣኔ ውስጥ ያላቸው ሚና ትልቅ ነው። ኢትዮጵያ አሁንም በአፍሪካ አንድነት እና መረጋጋት ውስጥ እንደ ቁልፍ ምሰሶ ትታያለች። በአኅጉሪቱ ውስጥ ያላት ድርሻ በታሪክ ሥር የሰደደ እና አሁን ባለው ዘመን በዲፕሎማሲ፣ በሰላም ግንባታ እና ልማት ሥራ በግልጽ ጎልቶ ይታያል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የፖለቲካ መዲና እንዲሁም የአይበገሬነት እና የነጻነት ምልክት ናት። አፍሪካ አንድነቷን ለማረጋገጥ፣ የተረጋጋ አኅጉር ለመፍጠር እና በራስ ዐቅም ነገሮችን የመከወን ጉዞ ትልም ውስጥ የኢትዮጵያ ድርሻ ቁልፍ ነው።   39ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ “ዘላቂ የውኃ ኑረትና ንጽህና ሥርዓት፤ ለአጀንዳ 2063 ስኬት” በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬና ነገ በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። ጉባዔው ኢትዮጵያ አኅጉራዊ የፖለቲካ እና ዲፕሎማሲያዊ መድረክ መሆኗን ዳግም የምታሳይበት ነው።
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!!
Feb 6, 2026 318
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በያንተስራ ወጋየሁ -ዲላ ቀን ቀንን እየወለደ ጊዜ ሳያቋርጥ እንደ ዥረት መፍሰሱን አያቆምም። ትናንት አዲስ የነበረው አሮጌው የሚባልበት፣ ዛሬ አዲስ ሆኖ ነገ አሮጌ ለመባል ይሮጣል። ወቅቶች ይፈራረቃሉ፣ ይመሻል፣ ይነጋል፣ ትናንት ለዛሬ፣ ዛሬ ለነገ እንዲህ እንዲህ እየተቀባበሉ ዘመን ዘመንን እየተካ ዛሬ ላይ ተደርሷል።   በጥምር ግብርናውና በቡናው የሚታወቀው ጌዴኦ ትናንትን ሸኝቶ ዛሬን እንደ አዲስ ለመቀበል ሽር ጉድ እያለ ነው። በክረምቱ የተዘራው ሰብል ተሰብስቦ ወደ ጎተራ እንዳስገባ ጌዴኦ አዲስ ዓመቱን ‹‹ዳራሮ››ን ይቀበላል። ዳራሮ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ቂም የያዘ ቂምና ቁርሾውን የሚተውበት፣ ወጣቶች የሚተጫጩበት፣ አዛውንቶች ወደ ሽምግልና የሚሸጋገሩበት እሴቶችን በውስጡ የያዘ ነው።   "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው የጌዴኦ አርሶ አደር ካመረተው ምርት ለመሪው፣ ልጆች ለወላጆችና ለአሳዳጊዎቻቸው፣ አዲስ ተጋቢዎች ለአማቾቻቸው፣ ቂም የያዘ ሰው እንዲሁ የተቀየመውን ሰው ይቅርታ ለመጠየቅ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። "ጉማታ" በጌዴኦ ዘመን መለወጫ ወቅት የሚፈጸም ስጦታ ነው። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማኅበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ነው። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። በዳራሮ በዓል አከባበር ውስጥ "ጉማታ" እጅግ አስፈላጊና ትልቅ ትርጉም ያለው ባህላዊ የክብር ስጦታ የመስጠት ሥርዓት ነው። "ጉማታ" ማለት በቀጥታ ትርጉሙ "ስጦታ" ማለት ቢሆንም፣ በጌዴኦ ባህል ግን ከስጦታ በላይ ነው። ምስጋናን፣ ፍቅርን፣ አክብሮትንና በረከትን የመጋራት መገለጫ ነው።   የጌዴአ ባህላዊ የባሌ ስርዓት መሪ ሆነው የሚሰየሙት አባ ገዳ ለህዝብ ከመጸለይ፣ ከማስታረቅና ክፉን በማውገዝ ህዝቡ ተፈጥሮን እንዲንከባከብ ከማስተማር ውጭ አይዘሩም፣ አይነግዱም፣ አልፎም እንሳስትን አያረቡም፡፡ የዳራሮ በዓልን ተከትሎ ህዝቡ የሚያቀርብላቸውን "ጉማታ" በመቀበል ባህላዊ የመሪነት ሚናቸውን በአግባቡ ከመወጣት ውጪ። ኑሮው ከጥምር እርሻ ጋር የተቆራኘው የጌዴኦ ሕዝብ ዘርቶ ካጨደው፣ አርብቶ ካገኘው ከብት፣ አንቦ ከቆረጠው ማር፣ ከሁሉም በአይነት በአይነቱ ሸክፎ ዳራሮ ወደ ሚከበርበት ሶንጎ (አደባባይ) ይተማል። ለጉማታ ከሚቀርቡ ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው ስጦታዎች አንዱ ማር ነው። ማር በጌዴኦ ዘንድ የጣፋጭ ዘመንና የጤና ምልክት ተደርጎ ይወሰዳልና ዋናው ስጦታ ነው። ጌዶኦዎች ቡና፣ ቅቤና ባህላዊ ምግቦች፣ የቁም እንስሳት በግና ስንጋ እንዲሁም ገንዘብ በመያዝ በበዓሉ ውስጥ የጉማታ ስርዓት ሲደርስ ተሽቀዳድመው ለአባ ገዳው በመስጠት ምርቃት ይቀበላሉ።   "ጉማታ" የተቀበለው ሰው የሚመርቀው ምርቃት በሰጪው ሕይወት ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይታመናልና ከስጦታው ይልቅ ምርቃቱ ትልቅ ዋጋ አለው። "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው ጌዴኦ በረከትን ማካፈል ለቀጣዩ ዓመት ተጨማሪ በረከት እንደሚያገኝ ስለሚያውቅ ጉማታ መስጠት የዘመናት ቅርሱ ነው። ጉማታ ከአባ ገዳና ከባህል ሽማግሌዎች ባለፈ አርሶ አደሩ ከማጋኖ (ከፈጣሪ) ያገኘውን በረከት ለሚወዳቸውና ለሚያከብራቸው ሰዎች የሚያቀርብበት መንገድ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ገልጸዋል።   ልጆች ለወላጆቻቸውና ለቤተሰብ አባላት ላሳደጓቸውና ለሰጧቸው ምርቃት ምስጋናቸውን ለመግለጽ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። በቅርቡ ጋብቻ የመሠረቱ ወጣቶች ወደ አማቾቻቸው ቤት ጉማታ ይዞ በመሄድ ዝምድናቸውን ያጠናክራሉ። በዓመቱ ውስጥ ቅሬታ ወይም ቂም ካለ፣ በዳራሮ ወቅት ጉማታ ይዞ በመሄድ ይቅርታ ይጠየቃል። ጉማታ የሰውን ልብ ለማለስለስና አዲስ ዓመትን በሰላም ለመጀመር ያገለግላል ተብሎ ስለሚታመን። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማህበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ስለመሆኑም ነው ዋና አስተዳዳሪው የጠቆሙት። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። ይህም የመደጋገፍ እሴትን ከማጠናከር በተጓዳኝ ህዝቡ የመንግስት ገቢን እንዲሁም በማህበረሰብ ተሳትፎ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆን መሰረት የጣለ ነው ይላሉ።   የዘንድሮው ዳራሮ ከቤት በተለይም ከአባ ገዳው መኖሪያ አንስቶ በሶንጎዎችና በየደረጃው በሚገኙ መዋቅሮች በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ጭምር እየተከበረ መሆኑን ያነሱት አስተዳዳሪው ጉማታም ዋናው የበዓሉ እሴት ሆኖ እየተከበረ ነው ብለዋል። ባህልና ማንነትን በማስጠበቅና በማዳበር፣ ባህሉ ወደ ወጣቶች እንዲተላለፍ በማበረታታት እንዲሁም የጌዴኦ ባህልን ለሌሎች ህዝቦች ለማስተዋወቅና የማህበረሰብ አንድነትና ባህላዊ እሴትን ለማጠናከር እያገለገለ ያለው የጌዴኦ ዘመን መለወጫ ዳራሮ ጥር 29 እና 30 በዲላ ከተማ ይከበራል። የዳራሮ በዓል የጌዴኦን ሕዝብ የሥራ ባህል፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ዕውቀትና የሰላም እሴት ለዓለም የሚያሳይ ትልቅ አጋጣሚ ነው። ይህ በዓል በተለይ የጌዴኦ የባህላዊ መልክዓ ምድር (Cultural Landscape) በዩኔስኮ (UNESCO) በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ተከትሎ፣ አሁን ላይ ከቤትና ከአደባባይ አልፎ ዓለም አቀፋዊ ትኩረት እያገኘ ያለ ታላቅ እሴት ሆኗል። የዓመት ሰው ይበለን!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም