ስፔን አርጀንቲናን በመርታት የዓለም ዋንጫን አነሳች - ኢዜአ አማርኛ
ስፔን አርጀንቲናን በመርታት የዓለም ዋንጫን አነሳች
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋለች።
ማምሻውን በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ግብ ሳይቆጠርበት በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
የአርጀንቲና የአማካይ ተጫዋች ኤንዞ ፈርናንዴዝ በ93ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
በ90 ደቂቃ አሸናፊ ባለመገኘቱ ቡድኖቹ ወደ ጭማሪ ሰዓት አምርቷል።
ተቀይሮ የገባው ፌራን ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል።
በጨዋታው ስፔን ፍጹም የበላይነት ወስዳለች።
የአርጀንቲናው ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ በርካታ ያለቀላቸው ኳሶችን አድኗል።
ተጋጣሚዋ አርጀንቲና በጨዋታው ደካማ እንቅስቃሴ አድርጋለች። ቡድኑ የግብ እድል መፍጠር ተስኖታል።
ውጤቱን ተከትሎ ስፔን ለሁለተኛው የዓለም ዋንጫን አንስታለች።
አውሮፓዊቷ ሀገር እ.አ.አ በ2010 ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 19ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ እንደነበረች ይታወሳል።
አርጀንቲና የዓለም ዋንጫ ክብሯን ማስጠበቅ አልቻለችም።
ለአራተኛ ጊዜ ዋንጫ የማንሳት ህልሟ አልተሳካም።