ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርጥ የዘላቂ የደን ልማት አለም አቀፍ እውቅና አገኘ
Oct 15, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርጥ የዘላቂ የደን ልማት አያያዝና አጠቃቀም በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) እውቅና አግኝቷል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ እውቅናውን ያገኘችው በጣሊያን ሮም እየተካሄደ ባለው የዓለም ምግብ ጉባዔ ላይ ነው። የዓለም የምግብ ጉባኤውም የምስረታ በዓሉ አካል ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ ሀገራት ተሳትፈዋል። ድርጅቱ ለኢትዮጵያ "በአረንጓዴ አሻራ ዘላቂ የደን ልማት አያያዝና አጠቃቀም" በሚል ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና የሰጠ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግስትን ወክለው የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ሽልማቱን ተቀብለዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በመርሃ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ፋኦ ርሃብን ለማጥፋት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስና የአካባቢ ጥበቃን ለማጠናከር ላለፉት 80 ዓመታት የላቀ አሻራ ማሳረፉን አንስተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ዛሬ በምርጥ የዘላቂ የደን ልማትና ጥበቃ ምሳሌነት እውቅና በማግኘቱ ኮርተናል ብለዋል። በመርሃ ግብሩ በብዙ ቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋንን ከ17 ነጥብ 2 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደጉን ተናግረዋል። ይህ በመሪ ግልፅ ራዕይና በህዝብ ጠንካራ ተሳትፎ የተሳካና ተስፋችንን ያለመለመ ስኬት ነው ያሉት ሚኒስትሯ፥ ይህንን ተጨባጭ ሥራ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እንዲጎበኙና በዓይን አይተው እንዲመሰክሩም ጋብዘዋል። ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ጋር ላለው ለረጅም ጊዜ የጸና አጋርነት ያመሰገኑት ሚኒስትሯ በጋራ ጥረታችን ችግኞችን እየተከልን የተሻለ ነገን ለልጆቻችን መገንባት ጀምረናል ብለዋል። የዓለም የምግብና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ) ከዚህ ቀደም በምግብ ዋስትና፣ በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦትና በስንዴ ምርት የላቀ አፈጻጸም ላሳዩት ቁርጠኝነት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሸለሙ ይታወሳል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዓለም የምግብና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ) 80ኛ የምስረታ ዓመት የድርጅቱን ያለፉት ዓመታት ስራዎች በሚዳስሱ እንዲሁም ቀጣይ ራዕዩን በሚገልጡ ዝግጅቶች እያከበረ ይገኛል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ለልማት ሥራዎች መፋጠን ተሳትፏችንን እናጠናክራለን - ባለሀብቶች
Oct 15, 2025 52
ጋምቤላ፤ ጥቅምት 5/ 2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለተጀመሩ የልማት ሥራዎች መፋጠን ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በተለያዩ የንግድና የኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩ ባለሃብቶች ገለጹ። በክልሉ የልማትና የንግድ እንቅስቃሴ ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ተጠናቋል ። ከውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች መካከል በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት ባለሃብት አቶ ኡሞድ ኡገር እንደገለጹት በክልሉ ለተጀመሩ የኮሪደርና ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ የልማት ሥራዎች መሳካት የበኩላቸውን ተሳትፎ ለማድረግ ዝግጁ ናቸው። የአቅመ ደካማ ቤቶችን መገንባትን ጨምሮ በሌሎች የልማት ስራዎች ሲሳተፉ መቆየታቸውን የገለጹት ደግሞ በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት አቶ ንጉስ በራ ናቸው። በቀጣይም በክልሉ በተጀመሩ የኮሪደርና ሌሎች ስራዎች ተሳትፏቸውን ይበልጥ አጠናከረው ለመቀጠል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሌላዋ በሆቴል ስራ የተሰማሩት ወይዘሮ አምሳለ ገብረወልድ በሰጡት አስተያየት የንግዱ ማህበረሰብ በክልሉ የሰላምና የልማት ስራዎች ተሳትፏችንን እናጠናክራለን ብለዋል ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንዳሉት ለክልሉ ልማትና እድገት መፋጠን የባለሀብቱ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ። የንግዱ ማህበረሰብና ባለሀብቱ በልማት ስራዎች ተሳትፏቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ሪፎርም እና የልማት ስራ ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል-የባንኩ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ
Oct 15, 2025 106
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ሪፎርም እና የልማት ስራ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የባንኩ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ አስታወቁ። የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) አመታዊ ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ነው። በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በዓመታዊው ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። ልዑካን ቡድኑ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ያካተተ ነው። የመንግስት ከፍተኛ ልዑካን ቡድኑ ከዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ ጋር ተወያይቷል። የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ልማት ያደረገውን የረጅም ጊዜ እና ዘርፈ ብዙ ድጋፍ አድንቀዋል። ባንኩ ለኢትዮጵያ ቁልፍ የኢኮኖሚ ዘርፎች ያለው አጠቃላይ የፋይናንስ ማዕቀፍ ከ16 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሻገሩን አመልክተዋል። ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ጠንካራ የኢኮኖሚ እድገት፣የወጪ ንግድ እና ሬሚታንስ እድገት፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማደግ እና የዋጋ ንረት መቀነስ በሪፎርሙ ከተገኙ ውጤቶች መካከል እንደሚጠቀሱ አንስተዋል። በውይይቱ አቶ አሕመድ፥ የኢትዮጵያ መንግስት ቁልፍ የልማት የትኩረት መስኮችን አንስተዋል። የግብርና ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን፣ የሰው ሀብት ልማት ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የግል የፋይናንስ ሀብት ማሰባሰብ፣ አማራጭ የፋይናንስ መፍትሄዎች መፈለግ እንዲሁም ቀጣናዊ እንዲሁም የባለብዙ ወገን ትብብርን ማጠናከር ሚኒስትሩ ያነሷቸው የትኩረት አጀንዳዎች ናቸው። የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ፥ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት እያደረገቻቸው ያሉ ጠንካራ እና ታሪካዊ የኢኮኖሚ ሪፎርሞችን አድንቀዋል። ፕሬዝዳንቱ የኢትዮጵያን ሀገራዊ ምክክር ያደነቁ ሲሆን ሂደቱ ማህበራዊ ትስስርን በማጠናከር ኢትዮጵያ አቅሟን ተጠቅማ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ እድገት እንድታስመዘግብ የሚያስችል ቁልፍ እርምጃ እንደሆነ ተናግረዋል። የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ የልማት ጉዞ፣ የሪፎርም አጀንዳ እና የልማት የትኩረት መስኮችን ለመደገፍ ቁርጠኛ ነው ብለዋል። የማክሮ ኢኮኖሚ ሂደቱ ዘላቂ የሆነ የልማት ውጤት እንዲያመጣ ድጋፉን እንደሚያደርግ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
በ2018 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 75 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በማሕበረሰብ ጤና መድህን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዷል- ጤና ቢሮ
Oct 15, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦በ2018 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 75 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በማሕበረሰብ ጤና መድህን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ የህብረተሰብ ጤና መድህን አባልነት አዲስ ምዝገባ፣ የነባር አባላት እድሳት እና አጠቃላይ አፈፃፀምን በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ቢሮው የህብረተሰቡን ጤና አጠባበቅ ለማጎልበት ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ዋነኛው መሆኑን ገልፀዋል። በዚህም ባለፈው ዓመት በተሰሩ ስራዎች አመርቂ ውጤት መመዝገቡን በማንሳት፥ በመዲናዋ በ2017 ዓ.ም ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆናቸውን ተናግረዋል። በጤና ጣቢያና በሆስፒታሎች ከ2 ነጥብ 83 ሚሊዮን በላይ አባላትና ቤተሰቦቻቸው ከቀላል እስከ ከፍተኛ የህክምና አገልግሎቶችን ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ይህም ፍትሐዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን እያረጋገጠ ነው ብለዋል። በ2018 ዓ.ም የነባር አባላት እድሳት በማካሄድ እና 10 በመቶ አዳዲስ አባላትን በመጨመር ከ2 ነጥብ 75 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም እስከ ህዳር 30 ቀን 2018 የሚቆይ የነባርና አዲስ የጤና መድህን አባላት ምዝገባ መጀመሩን አስረድተዋል። መክፈል የሚችሉ የህብረተሰብ ክፍሎች አቅማቸውን ባገናዘበ ዓመታዊ መዋጮ በመክፈል የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አባል እንደሚሆኑ ተናግረዋል። በከተማ አስተዳደሩ የፀደቀው የነባርና አዲስ አባል መደበኛ ዓመታዊ መዋጮ ከ1 ሺህ 500 እስከ 10 ሺህ 500 ብር መሆኑን ጠቅሰው የመመዝገቢያ 200 ብር መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል። በዝቅተኛ የኑሮ ሁኔታ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ደግሞ ወጪውን ከተማ አስተዳደሩ እንደሚሸፍን ጠቁመዋል። ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆኑ ልጆች እና የቤተሰብ አባላት ያላቸውም በእያንዳንዱ ሰው ተጨማሪ 50 በመቶ በመክፈል አባል ማድረግ እንዳለባቸው ነው የጠቆሙት፡፡ ህብረተሰቡ ራሱንና ቤተሰቡን ካልታሰበ ድንገተኛ ወጪ ለመጠበቅ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆን እንዳለበትም ነው ያስገነዘቡት፡፡
የመሰረተ ልማት ስራዎች ተጠብቀው የዜጎች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ህግ የማስከበር ስራችንን እናጠናክራለን - ፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት
Oct 15, 2025 95
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፡-በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ የመሰረተ ልማት ስራዎች ተጠብቀው የዜጎች ተጠቃሚነትን የበለጠ ለማረጋገጥ ህግ የማስከበር ተግባራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት ገለጹ። የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት ከእንጦጦ ፓርክ እስከ አቃቂ ቃሊቲ ድረስ የተሰሩ የኮሪደር ልማት እና ልዩ ልዩ መሰረተ ልማቶች ስራዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት እንደገለጹት፤ በከተማዋ በተገነቡ መሰረተ ልማት ስራዎች እጅግ ተደንቀዋል። በፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ጤና አገልግሎት ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አብደላ አደላ፤ አዲስ አበባን ጨምሮ በመላው አገሪቷ እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ስራዎች የሰላም ፍሬ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። የአገር ልማት የሚረጋገጠው ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ሲሰፍን ብቻ መሆኑን ጠቁመው፤ "ሰላምና ልማት የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው" ብለዋል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ሰላምን የማስጠበቅና ልማትን እንዲፋጠን የማድረግ ተግባርን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው የተናገሩት፡፡ በፌዴራል ፖሊስ ሆስፒታል የግዥ ሃላፊ ኮማንደር ባዬ ሽፈራው በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የከተማዋ ውበት፣ መሰረተ ልማቶች አገሪቷ ፈጣን እድገት ውስጥ መሆኗን አመላካቾች ናቸው። ፖሊስ የልማት አደናቃፊ እና የፀረ ሰላም ሃይሎችን እኩይ ተግባር እያከሸፈ መምጣቱን አውስተው፤ ይህን ተግባሩን ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ በፌዴራል ፖሊስ የልዩ ፀረ ሽብር ኮማንዶ አባል ዋና ኢንስፔክተር አየለ አሸናፊ፤ በዛሬው ጉብኝታችን አገራችን እየተጓዘችበት ያለውን ከፍታ በተግባር ያየነበትና ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ረዳት ኢንስፔክተር ማርታ ወረቁ በበኩላቸው፤ የህዝብንና የአገርን ሰላም ለማረጋገጥ የሚከፈለው ዋጋ ለዚህ ዓይነት የልማት ስራዎች አብቅቶናል ብለዋል። በፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ተቋም ጥበቃ መምሪያ የሬጅመንት አዛዥ ኮሎኔል ማቲዮስ ሸጋው እንደገለጹት፤ ፖሊስ ህዝብና መንግስት በሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች የራሱን አሻራ የማኖር ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ፖለቲካ
የአፍሪካ ህብረት፣ ኢጋድ እና የሀገራት መሪዎች በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ
Oct 15, 2025 137
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018(ኢዜአ):- የአፍሪካ ህብረት፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) እና የሀገራት መሪዎች በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ሞት ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በሀዘን መልዕክታቸው ራይላ ኦዲንጋ በኬንያ ፖለቲካ ውስጥ ትልቅ ስፍራ የነበራቸውና የዴሞክራሲ፣ የመልካም አስተዳደርና ህዝብ ተኮር የልማት ስራዎች መገለጫ ናቸው ብለዋል። ኦዲንጋ የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት ከፍተኛ ተወካይ በነበሩበት ወቅት ለአፍሪካ የትስስር አጀንዳ መሳካት አበክረው መስራታቸውን ያወሱት ሊቀ መንበሩ ለአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና እና ለአህጉራዊ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ትራንስፎርሜሽን ስራዎች አስተዋጽኦ ማድረጋቸውንም አመልክተዋል። አፍሪካ ባለ ራዕይ ልጇን አጥታለች፤ የኦዲንጋ አሻራ የበለጸገች፣ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊት አህጉር የመገንባር የጋራ ጥረታችንን በጽናት እንድንቀጥል መነሳሳትን ይፈጥርልናል ነው ያሉት። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ለራይላ ዲንጋ ቤተሰብ፣ ለኬንያ ህዝብና መንግስት እንዲሁም ለአፍሪካውያን በሙሉ መጽናናትን ተመኝተዋል። በተመሳሳይ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። በሀዘን መግለጫ መልዕክታቸውም ራይላ ኦዲንጋ ጠንካራ ፓን አፍሪካዊ እና ህይወታቸውን በሙሉ ለዴሞክራሲ፣ ለፍትህ እና ለአንድነት መታገላቸውን አውስተዋል። ኦዲንጋ ያደረጉት የእድሜ ዘመን የነጻነት እና እኩልነት ትግል ከኬንያ አልፎም በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በትውልዶች መካከል የተሻገረ እና መነሳሳትን የፈጠረ ነው ብለዋል። ኢጋድ በዚህ ጥልቅ የሀዘን ወቅት ከኬንያ ህዝብ እና መንግስት ጋር ይቆማል ያሉት ዋና ፀሐፊው ኦዲንጋ ሁሌም የዴሞክራሲ መሰረት ለመጣል እና በአፍሪካ የነገ መለወጥ ላይ ጠንካራ እምነት እንዲገነባ ባበረከቱት አስተዋጽኦ ሁሌም ሲታወሱ እንደሚኖሩ አመልክተዋል። የኦዲንጋ ተምሳሌታዊ ተግባር ነጻ እና የበለጠ አንድ የሆነች አፍሪካ የመፍጠር ራዕይ የማሳካት ጉዞ አቅም ሆኖ እንደሚቀጥል አምናለሁ ሲሉም ገልጸዋል። በተጨማሪም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የጅቡቲ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ፣ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ማሃሙድ እና የታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን፣ የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በራይላ ኦዲንጋ ህልፈተ ህይወት ሀዘናቸውን ከገለጹ የሀገራት መሪዎች መካከል ይገኙበታል። የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ በልብ ሕመም ምክንያት በህንድ ህክምና ሲከታተሉ ቆይተው በ80 ዓመታቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ የተጀመረው ልማት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላችንን እየተወጣን ነው - የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች
Oct 15, 2025 134
ገንዳ ውሃ ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):- የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በአማራ ክልል የህግ የበላይነት በማስከበር የሰፈነውን ሰላም ለማፅናት ሲከናወን የቆየው ሕብረተሰቡን ያሳተፈ ተግባር ውጤታማ መሆኑ ተመልክቷል። በተሳሳተ መንገድ ችግር ውስጥ ገብተው የነበሩ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማሕበረሰቡ ተቀላቅለዋል። በክልሉ የሰፈነውን ሰላም ለማፅናት እየተከናወነ ባለው ተግባር እየተሳተፉ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ካሉት ውስጥ በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች ይገኙበታል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ወዳጅ ደሳለኝ፤ በሀገራችን ታላቁ የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ደማቅ ታሪክ እየተጻፈ ይገኛል ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል። የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁላችንም በያለንበት አካባቢ ከመንግስት ጎን ተሰልፈን ሰላምን በማስጠበቅ የጀመርነውን ተግባር ማስቀጠል አለብን ብለዋል። መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ እየተመለሱ ያሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የበደሉትን ሕዝብ በመካስ ሰላም ጸንቶ እንዲቀጥል የድርሻቸውን እንዲወጡ የሚደግፉ መሆኑን ገልጸዋል። የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ልማት እንዲጠናከር ከመንግስት ጎን ተሰልፈው የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንም ተናግረዋል። ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ብሩክ ወርቄ በበኩላቸው፤ ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ልንጠብቀው ይገባል ብለዋል። ሰላም በአንድ ወገን ብቻ ሊፀና እንደማይችል በመገንዘብ ሰላምንና ልማትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ከመንግስት ጎን ተሰልፈው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የተገኘውን ሰላም በማፅናት የልማትና የመልካም አስተዳደር ሰራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ አለምነሽ አዛናው ናቸው። ነዋሪዎቹ ፤የፅንፈኝነት አስተሳሰብን አጥብቀው እንደሚቃወሙ አንስተው፤ የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላምን በመጠበቅ ልማትን ለማፋጠን ከመንግስት ጎን ተሰልፈው የበኩላቸውን መወጣታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።
ለሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬታማነት ህዝብን ለልማት የማስተባበር ሀላፊነታችንን እንወጣለን-የምክር ቤት አባላት
Oct 15, 2025 121
ሚዛን አማን፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):- ለሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬታማነት ህዝብን ለልማት የማስተባበር ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት አባላት ገለጹ። የዜጎችን ፍትሃዊ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስና ሀገራዊ እድገትን ለማፋጠን በመንግስት የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ተናግረዋል። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አቶ መንግስቱ መኩሪያ እንዳሉት በክልሉ እየታዩ ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ለውጦች ተስፋ የሚሰጡ ናቸው። እንደ ሀገር የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶችም የክልሉን ሕዝብ በልማት ተጠቃሚ የሚያደርጉ በመሆኑ ስኬታማ እንዲሆኑ ህዝብን በማስተባበር የድርሻቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሳየውን ትብብርና አንድነት አሁን ለተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶችም በማሳየት የበኩሉን እንዲወጣ የማስገንዘብና የማስተባበር ሚናቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል። ሕዝብን በአንድነት አስተባብሮ መስራት ከተቻለ የባህር በርን ጨምሮ የማይሳካ የልማት ጥያቄ አይኖርም ያሉት ደግሞ ሌላው የምክር ቤቱ አባል አቶ ካጁ አቤል ናቸው። ሀገራዊ ለውጡ እንዲጠናከርና ልማትን ለፋጠን የተጀመሩ ሜጋ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ስኬታማ እንዲሆኑ የዜጎች ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት አቶ ካጁ፣ ህብረተሰቡ የልማት ትብብሩን እንዲያጠናክር በሕዝብ ተወካይነታቸው የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። የዜጎችን ፍትሃዊ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስና ሀገራዊ እድገትን ለማፋጠን መንግስት የጀመራቸው የልማት ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ፕሮጀክት አርሶ አደሩ በአፈር ማዳበሪያ በየጊዜው ሲገጥመው የነበረውን ችግር እንደሚፈታ የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ አረጋሽ አዘዘው የተባሉ የምክር ቤቱ አባል ናቸው። የማዳበሪያ ፋብሪካውና ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የውጭ ምንዛሬ ወጪን ከማስቀረት ባለፈ ምርትና ምርታማነትና በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ ጠቀሜታ እንዳለውም አመልክተዋል። ፕሮጀክቶቹ ለሀገር ያላቸው ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ የጎላ በመሆኑ በጋራ ተረባርቦ ማሳካት እንደሚገባና ለዚህም ህዝብን ከማስተባበር ጀምሮ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። በክልሉ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች የብሔረሰቦች ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መምጣቱንና ክትትላቸውን እንደሚያጠናክሩ የገለጹት ደግሞ ሌላው የምክር ቤት አባል አቶ ቢልልኝ ወልደሰንበት ናቸው። በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በተለያየ መንገድ ሀገርና ህዝብን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ገልጸው፣ የህዝብን አብሮነትና የልማት ተሳትፎ ለሚያጠናክሩ ተግባራት ትኩረት እንደሚሰጡ ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ትናንት በቴፒ ከተማ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈት ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ
Oct 15, 2025 113
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈት ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በራይላ ኦዲንጋ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸው ጥልቅ መጽናናትን ተመኝተዋል።
አምባሳደሮች በኢትዮጵያ እና በሀገሮቻቸው መካከል ሁለንተናዊ ግንኙነትን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል - ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Oct 14, 2025 196
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች በኢትዮጵያ እና በሚወክሏቸው ሀገራት መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ግንኙነት ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ የተለያዩ ሀገራት አዲስ ተሿሚ አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። የሹመት ደብዳቤያቸውን ካቀረቡ አምባሳደሮች መካከል የሞሪታኒያ፣ የካዛኪስታን፣ የቫቲካን፣ የባንግላዲሽ፣ የዐረብ ሊግ፣ የኢንዶኔዥያ፣ የሰርቢያ፣ የስዊድን፣ የካናዳ፣ የሲውዘርላንድ እና የግብጽ አምባሳደሮች ይገኙበታል። ሁነቱን የተከታተሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ አምባሳደሮቹ የሹመት ደብዳቤያቸውን ባቀረቡበት ወቅት ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ከሀገራቱ ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ የማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ፕሬዝዳንቱ መግለጻቸውን ተናግረዋል። አምባሳደሮቹ በሥራ ዘመናቸው በኢትዮጵያና በሚወክሏቸው ሀገራት መካከል ሁለንተናዊ ግንኙነት እንዲጎለብትና እንዲጠናከር መስራት እንዳለባቸውም አፅንኦት መስጠታቸውን ጠቁመዋል። ፕሬዝዳንቱ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም እያከናወነች መሆኑን ማውሳታቸውን ጠቁመው፤ አምባሳደሮቹ በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በቱሪዝም ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር ለማስተሳሰር ጥረት እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። ኢንቨስተሮች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በተፈጠረው ምቹ የኢኮኖሚ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሳተፉ ባለሀብቶችን ማበረታታት እንዳለባቸውም እንዲሁ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ አሁን ላይ እያሳየች ያለው የኢኮኖሚ እና የመሰረተ ልማት እድገት በሁሉም ዘርፍ ትብብርን ለማጎልበት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ብለዋል። በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂ፣ በማዕድን ልማት፣ በኢንቨስትመንትና በሌሎችም ዘርፎች የጋራ ተጠቃሚነትን ማዕከል ያደረገ ትብብርን እንደሚያጠናክሩም አረጋግጠዋል።
ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ሊፈቱ የሚገባው በሁለቱ አገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Oct 14, 2025 217
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙትን የግብጽ አምባሳደር አባይዳ ኤ ኤል ዳንዳራዊን የሹመት ደብዳቤ ዛሬ ተቀብለዋል። ኢዜአ ከፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ፕሬዝዳንቱ ከአምባሳደሩ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ በሁለቱ ሃገራት መካከል ለረጅም ጊዜ የቆየውን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት አንስተዋል። በሁለቱ አገራት መካከል ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ቢኖሩም በሁለቱ ሃገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ የሚደረስባቸው መሆኑንም አስረድተዋል። አገራቱ ግንኙነታቸውን ግብርናን ጨምሮ በኢንዱስትሪ፣ በማኑፋክቸሪንግና በሌሎች በርካታ ዘርፎች መቀጠል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ
Oct 14, 2025 184
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ዛሬ ተቀበሉ። ፕሬዚዳንቱ ዛሬ በብሔራዊ ቤተ መንግስት በተካሄደው ሥነ ስርዓት ላይ የተለያዩ አገራትን አዳዲስ አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀብለዋል። ለፕሬዚዳንት ታዬ የሹመት ደብዳቤያቸወን ካቀረቡት መካከል የሞሪታኒያ አምባሳደር ኢል ሀውሴን ኦልድ ናጊ፣የካዛኪስታን አምባሳደር ዣልጋስ አዲልባየቭ ፣ የቫቲካን አምባሳደር ብሬን ኦዲጊግዊ፣የባንግላዲሽ አምባሳደር ኤር ቫይስ ማርሻል ሲትዋት ናዬም እና የዐረብ ሊግ አምባሳደር መሐመድ ኦማር አል ማርሆን ይጠቀሳሉ። በተመሳሳይ የኢንዶኔዥያው አምባሳደር ፋይዝል ቸሪይ ሲዳርት፣ የሰርቢያ አምባሳደር ዳቮር ትርኩልጃ እና የስዊድኑ አምባሳደር ማኙስ ሌናርትሶን የሹመት ደብዳቤያቻውን አቅርበዋል። በተጨማሪም የካናዳው አምባሳደር ኒኮላስ ሲማርድ፣ ሲውዘርላንድ አምባሳድር ሪካረድ ቻንዳ፣ የግብጹ አምባሳደር ኦባይዳ ኢል ዳንዳራውይ፣ የሀንጋሪው አምባሳደር አቲላ ቶዝ፣ ሳን ማሪያኖ አምባሳደር ፔሮ ስካርፔሊኒ እና የቱሪክሜንስታን አምባሳደር መካን ኢሻነጉሊየብ የሹመት ደብዳቤያቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለአምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የስራ መመሪያ ሰጡ
Oct 14, 2025 177
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ለተመደቡት አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን ተመድበዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን ከፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በመቀበል በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መኃላ ፈፅመዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለአምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ እና ጅቡቲን ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ የሥራ መመሪያ መስጠታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ ተገኝተዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) ከዚህ ቀደም የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ሆነው ማገልገላቸው ይታወቃል።
ፖለቲካ
የአፍሪካ ህብረት፣ ኢጋድ እና የሀገራት መሪዎች በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ
Oct 15, 2025 137
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018(ኢዜአ):- የአፍሪካ ህብረት፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) እና የሀገራት መሪዎች በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ሞት ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በሀዘን መልዕክታቸው ራይላ ኦዲንጋ በኬንያ ፖለቲካ ውስጥ ትልቅ ስፍራ የነበራቸውና የዴሞክራሲ፣ የመልካም አስተዳደርና ህዝብ ተኮር የልማት ስራዎች መገለጫ ናቸው ብለዋል። ኦዲንጋ የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት ከፍተኛ ተወካይ በነበሩበት ወቅት ለአፍሪካ የትስስር አጀንዳ መሳካት አበክረው መስራታቸውን ያወሱት ሊቀ መንበሩ ለአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና እና ለአህጉራዊ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ትራንስፎርሜሽን ስራዎች አስተዋጽኦ ማድረጋቸውንም አመልክተዋል። አፍሪካ ባለ ራዕይ ልጇን አጥታለች፤ የኦዲንጋ አሻራ የበለጸገች፣ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊት አህጉር የመገንባር የጋራ ጥረታችንን በጽናት እንድንቀጥል መነሳሳትን ይፈጥርልናል ነው ያሉት። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ለራይላ ዲንጋ ቤተሰብ፣ ለኬንያ ህዝብና መንግስት እንዲሁም ለአፍሪካውያን በሙሉ መጽናናትን ተመኝተዋል። በተመሳሳይ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። በሀዘን መግለጫ መልዕክታቸውም ራይላ ኦዲንጋ ጠንካራ ፓን አፍሪካዊ እና ህይወታቸውን በሙሉ ለዴሞክራሲ፣ ለፍትህ እና ለአንድነት መታገላቸውን አውስተዋል። ኦዲንጋ ያደረጉት የእድሜ ዘመን የነጻነት እና እኩልነት ትግል ከኬንያ አልፎም በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በትውልዶች መካከል የተሻገረ እና መነሳሳትን የፈጠረ ነው ብለዋል። ኢጋድ በዚህ ጥልቅ የሀዘን ወቅት ከኬንያ ህዝብ እና መንግስት ጋር ይቆማል ያሉት ዋና ፀሐፊው ኦዲንጋ ሁሌም የዴሞክራሲ መሰረት ለመጣል እና በአፍሪካ የነገ መለወጥ ላይ ጠንካራ እምነት እንዲገነባ ባበረከቱት አስተዋጽኦ ሁሌም ሲታወሱ እንደሚኖሩ አመልክተዋል። የኦዲንጋ ተምሳሌታዊ ተግባር ነጻ እና የበለጠ አንድ የሆነች አፍሪካ የመፍጠር ራዕይ የማሳካት ጉዞ አቅም ሆኖ እንደሚቀጥል አምናለሁ ሲሉም ገልጸዋል። በተጨማሪም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የጅቡቲ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ፣ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ማሃሙድ እና የታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን፣ የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በራይላ ኦዲንጋ ህልፈተ ህይወት ሀዘናቸውን ከገለጹ የሀገራት መሪዎች መካከል ይገኙበታል። የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ በልብ ሕመም ምክንያት በህንድ ህክምና ሲከታተሉ ቆይተው በ80 ዓመታቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ የተጀመረው ልማት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላችንን እየተወጣን ነው - የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች
Oct 15, 2025 134
ገንዳ ውሃ ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):- የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። በአማራ ክልል የህግ የበላይነት በማስከበር የሰፈነውን ሰላም ለማፅናት ሲከናወን የቆየው ሕብረተሰቡን ያሳተፈ ተግባር ውጤታማ መሆኑ ተመልክቷል። በተሳሳተ መንገድ ችግር ውስጥ ገብተው የነበሩ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማሕበረሰቡ ተቀላቅለዋል። በክልሉ የሰፈነውን ሰላም ለማፅናት እየተከናወነ ባለው ተግባር እየተሳተፉ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ካሉት ውስጥ በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች ይገኙበታል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ወዳጅ ደሳለኝ፤ በሀገራችን ታላቁ የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ደማቅ ታሪክ እየተጻፈ ይገኛል ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል። የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁላችንም በያለንበት አካባቢ ከመንግስት ጎን ተሰልፈን ሰላምን በማስጠበቅ የጀመርነውን ተግባር ማስቀጠል አለብን ብለዋል። መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ እየተመለሱ ያሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የበደሉትን ሕዝብ በመካስ ሰላም ጸንቶ እንዲቀጥል የድርሻቸውን እንዲወጡ የሚደግፉ መሆኑን ገልጸዋል። የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ልማት እንዲጠናከር ከመንግስት ጎን ተሰልፈው የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንም ተናግረዋል። ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ብሩክ ወርቄ በበኩላቸው፤ ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ልንጠብቀው ይገባል ብለዋል። ሰላም በአንድ ወገን ብቻ ሊፀና እንደማይችል በመገንዘብ ሰላምንና ልማትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ከመንግስት ጎን ተሰልፈው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የተገኘውን ሰላም በማፅናት የልማትና የመልካም አስተዳደር ሰራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ አለምነሽ አዛናው ናቸው። ነዋሪዎቹ ፤የፅንፈኝነት አስተሳሰብን አጥብቀው እንደሚቃወሙ አንስተው፤ የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላምን በመጠበቅ ልማትን ለማፋጠን ከመንግስት ጎን ተሰልፈው የበኩላቸውን መወጣታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።
ለሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬታማነት ህዝብን ለልማት የማስተባበር ሀላፊነታችንን እንወጣለን-የምክር ቤት አባላት
Oct 15, 2025 121
ሚዛን አማን፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):- ለሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬታማነት ህዝብን ለልማት የማስተባበር ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት አባላት ገለጹ። የዜጎችን ፍትሃዊ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስና ሀገራዊ እድገትን ለማፋጠን በመንግስት የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ተናግረዋል። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አቶ መንግስቱ መኩሪያ እንዳሉት በክልሉ እየታዩ ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ለውጦች ተስፋ የሚሰጡ ናቸው። እንደ ሀገር የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶችም የክልሉን ሕዝብ በልማት ተጠቃሚ የሚያደርጉ በመሆኑ ስኬታማ እንዲሆኑ ህዝብን በማስተባበር የድርሻቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሳየውን ትብብርና አንድነት አሁን ለተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶችም በማሳየት የበኩሉን እንዲወጣ የማስገንዘብና የማስተባበር ሚናቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል። ሕዝብን በአንድነት አስተባብሮ መስራት ከተቻለ የባህር በርን ጨምሮ የማይሳካ የልማት ጥያቄ አይኖርም ያሉት ደግሞ ሌላው የምክር ቤቱ አባል አቶ ካጁ አቤል ናቸው። ሀገራዊ ለውጡ እንዲጠናከርና ልማትን ለፋጠን የተጀመሩ ሜጋ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ስኬታማ እንዲሆኑ የዜጎች ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት አቶ ካጁ፣ ህብረተሰቡ የልማት ትብብሩን እንዲያጠናክር በሕዝብ ተወካይነታቸው የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። የዜጎችን ፍትሃዊ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስና ሀገራዊ እድገትን ለማፋጠን መንግስት የጀመራቸው የልማት ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ፕሮጀክት አርሶ አደሩ በአፈር ማዳበሪያ በየጊዜው ሲገጥመው የነበረውን ችግር እንደሚፈታ የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ አረጋሽ አዘዘው የተባሉ የምክር ቤቱ አባል ናቸው። የማዳበሪያ ፋብሪካውና ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የውጭ ምንዛሬ ወጪን ከማስቀረት ባለፈ ምርትና ምርታማነትና በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ ጠቀሜታ እንዳለውም አመልክተዋል። ፕሮጀክቶቹ ለሀገር ያላቸው ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ የጎላ በመሆኑ በጋራ ተረባርቦ ማሳካት እንደሚገባና ለዚህም ህዝብን ከማስተባበር ጀምሮ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። በክልሉ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች የብሔረሰቦች ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መምጣቱንና ክትትላቸውን እንደሚያጠናክሩ የገለጹት ደግሞ ሌላው የምክር ቤት አባል አቶ ቢልልኝ ወልደሰንበት ናቸው። በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በተለያየ መንገድ ሀገርና ህዝብን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ገልጸው፣ የህዝብን አብሮነትና የልማት ተሳትፎ ለሚያጠናክሩ ተግባራት ትኩረት እንደሚሰጡ ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ትናንት በቴፒ ከተማ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈት ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ
Oct 15, 2025 113
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህልፈት ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በራይላ ኦዲንጋ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸው ጥልቅ መጽናናትን ተመኝተዋል።
አምባሳደሮች በኢትዮጵያ እና በሀገሮቻቸው መካከል ሁለንተናዊ ግንኙነትን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል - ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Oct 14, 2025 196
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች በኢትዮጵያ እና በሚወክሏቸው ሀገራት መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ግንኙነት ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ የተለያዩ ሀገራት አዲስ ተሿሚ አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። የሹመት ደብዳቤያቸውን ካቀረቡ አምባሳደሮች መካከል የሞሪታኒያ፣ የካዛኪስታን፣ የቫቲካን፣ የባንግላዲሽ፣ የዐረብ ሊግ፣ የኢንዶኔዥያ፣ የሰርቢያ፣ የስዊድን፣ የካናዳ፣ የሲውዘርላንድ እና የግብጽ አምባሳደሮች ይገኙበታል። ሁነቱን የተከታተሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ አምባሳደሮቹ የሹመት ደብዳቤያቸውን ባቀረቡበት ወቅት ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ከሀገራቱ ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ የማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ፕሬዝዳንቱ መግለጻቸውን ተናግረዋል። አምባሳደሮቹ በሥራ ዘመናቸው በኢትዮጵያና በሚወክሏቸው ሀገራት መካከል ሁለንተናዊ ግንኙነት እንዲጎለብትና እንዲጠናከር መስራት እንዳለባቸውም አፅንኦት መስጠታቸውን ጠቁመዋል። ፕሬዝዳንቱ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም እያከናወነች መሆኑን ማውሳታቸውን ጠቁመው፤ አምባሳደሮቹ በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በቱሪዝም ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር ለማስተሳሰር ጥረት እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። ኢንቨስተሮች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በተፈጠረው ምቹ የኢኮኖሚ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሳተፉ ባለሀብቶችን ማበረታታት እንዳለባቸውም እንዲሁ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ አሁን ላይ እያሳየች ያለው የኢኮኖሚ እና የመሰረተ ልማት እድገት በሁሉም ዘርፍ ትብብርን ለማጎልበት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ብለዋል። በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂ፣ በማዕድን ልማት፣ በኢንቨስትመንትና በሌሎችም ዘርፎች የጋራ ተጠቃሚነትን ማዕከል ያደረገ ትብብርን እንደሚያጠናክሩም አረጋግጠዋል።
ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ሊፈቱ የሚገባው በሁለቱ አገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Oct 14, 2025 217
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙትን የግብጽ አምባሳደር አባይዳ ኤ ኤል ዳንዳራዊን የሹመት ደብዳቤ ዛሬ ተቀብለዋል። ኢዜአ ከፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ፕሬዝዳንቱ ከአምባሳደሩ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ በሁለቱ ሃገራት መካከል ለረጅም ጊዜ የቆየውን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት አንስተዋል። በሁለቱ አገራት መካከል ቀሪ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ቢኖሩም በሁለቱ ሃገራት አቅም፣ የጋራ ጥረት እና ብልሃት ብቻ የሚደረስባቸው መሆኑንም አስረድተዋል። አገራቱ ግንኙነታቸውን ግብርናን ጨምሮ በኢንዱስትሪ፣ በማኑፋክቸሪንግና በሌሎች በርካታ ዘርፎች መቀጠል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ
Oct 14, 2025 184
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ዛሬ ተቀበሉ። ፕሬዚዳንቱ ዛሬ በብሔራዊ ቤተ መንግስት በተካሄደው ሥነ ስርዓት ላይ የተለያዩ አገራትን አዳዲስ አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤ ተቀብለዋል። ለፕሬዚዳንት ታዬ የሹመት ደብዳቤያቸወን ካቀረቡት መካከል የሞሪታኒያ አምባሳደር ኢል ሀውሴን ኦልድ ናጊ፣የካዛኪስታን አምባሳደር ዣልጋስ አዲልባየቭ ፣ የቫቲካን አምባሳደር ብሬን ኦዲጊግዊ፣የባንግላዲሽ አምባሳደር ኤር ቫይስ ማርሻል ሲትዋት ናዬም እና የዐረብ ሊግ አምባሳደር መሐመድ ኦማር አል ማርሆን ይጠቀሳሉ። በተመሳሳይ የኢንዶኔዥያው አምባሳደር ፋይዝል ቸሪይ ሲዳርት፣ የሰርቢያ አምባሳደር ዳቮር ትርኩልጃ እና የስዊድኑ አምባሳደር ማኙስ ሌናርትሶን የሹመት ደብዳቤያቻውን አቅርበዋል። በተጨማሪም የካናዳው አምባሳደር ኒኮላስ ሲማርድ፣ ሲውዘርላንድ አምባሳድር ሪካረድ ቻንዳ፣ የግብጹ አምባሳደር ኦባይዳ ኢል ዳንዳራውይ፣ የሀንጋሪው አምባሳደር አቲላ ቶዝ፣ ሳን ማሪያኖ አምባሳደር ፔሮ ስካርፔሊኒ እና የቱሪክሜንስታን አምባሳደር መካን ኢሻነጉሊየብ የሹመት ደብዳቤያቸውን አቅርበዋል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለአምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የስራ መመሪያ ሰጡ
Oct 14, 2025 177
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ለተመደቡት አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን ተመድበዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን ከፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በመቀበል በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መኃላ ፈፅመዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለአምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ እና ጅቡቲን ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር የሚያስችሉ የሥራ መመሪያ መስጠታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ ተገኝተዋል። አምባሳደር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) ከዚህ ቀደም የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ሆነው ማገልገላቸው ይታወቃል።
ማህበራዊ
በ2018 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 75 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በማሕበረሰብ ጤና መድህን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዷል- ጤና ቢሮ
Oct 15, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦በ2018 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 75 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በማሕበረሰብ ጤና መድህን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ የህብረተሰብ ጤና መድህን አባልነት አዲስ ምዝገባ፣ የነባር አባላት እድሳት እና አጠቃላይ አፈፃፀምን በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ቢሮው የህብረተሰቡን ጤና አጠባበቅ ለማጎልበት ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ዋነኛው መሆኑን ገልፀዋል። በዚህም ባለፈው ዓመት በተሰሩ ስራዎች አመርቂ ውጤት መመዝገቡን በማንሳት፥ በመዲናዋ በ2017 ዓ.ም ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆናቸውን ተናግረዋል። በጤና ጣቢያና በሆስፒታሎች ከ2 ነጥብ 83 ሚሊዮን በላይ አባላትና ቤተሰቦቻቸው ከቀላል እስከ ከፍተኛ የህክምና አገልግሎቶችን ማግኘታቸውን ተናግረዋል። ይህም ፍትሐዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን እያረጋገጠ ነው ብለዋል። በ2018 ዓ.ም የነባር አባላት እድሳት በማካሄድ እና 10 በመቶ አዳዲስ አባላትን በመጨመር ከ2 ነጥብ 75 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም እስከ ህዳር 30 ቀን 2018 የሚቆይ የነባርና አዲስ የጤና መድህን አባላት ምዝገባ መጀመሩን አስረድተዋል። መክፈል የሚችሉ የህብረተሰብ ክፍሎች አቅማቸውን ባገናዘበ ዓመታዊ መዋጮ በመክፈል የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አባል እንደሚሆኑ ተናግረዋል። በከተማ አስተዳደሩ የፀደቀው የነባርና አዲስ አባል መደበኛ ዓመታዊ መዋጮ ከ1 ሺህ 500 እስከ 10 ሺህ 500 ብር መሆኑን ጠቅሰው የመመዝገቢያ 200 ብር መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል። በዝቅተኛ የኑሮ ሁኔታ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ደግሞ ወጪውን ከተማ አስተዳደሩ እንደሚሸፍን ጠቁመዋል። ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆኑ ልጆች እና የቤተሰብ አባላት ያላቸውም በእያንዳንዱ ሰው ተጨማሪ 50 በመቶ በመክፈል አባል ማድረግ እንዳለባቸው ነው የጠቆሙት፡፡ ህብረተሰቡ ራሱንና ቤተሰቡን ካልታሰበ ድንገተኛ ወጪ ለመጠበቅ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆን እንዳለበትም ነው ያስገነዘቡት፡፡
በጤናው ዘርፍ እየተተገበረ የሚገኘው የመከላከልና የማከም ፖሊሲ አበረታች ውጤት እየታየበት ነው
Oct 15, 2025 65
ባሕርዳር፤ጥቅምት 5/ 2018 (ኢዜአ)፡-በጤናው ዘርፍ እየተተገበረ የሚገኘው የመከላከልና የማከም ፖሊሲ አበረታች ውጤት እየታየበት መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማሕበራዊ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ገለጹ። የአማራ ክልል ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በክልሉ የወባ መከላከልና መቆጣጠር ንቅናቄ መድረክ በባሕር ዳር ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማሕበራዊ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር)፤ በጤናው ዘርፍ እየተተገበረ የሚገኘው የመከላከልና የማከም ፖሊሲ አበረታች ውጤት እየታየበት መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ የወባ በሽታ ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም በማከም ረገድ እየተደረገ ያለው ቅንጅታዊ አሰራር ጥሩ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቀጣይም በክልሉ ለወባ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት ግንዛቤ የመፍጠር፣ የመከላከልና የማከም ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የክልሉ ጤና ቢሮ ኀላፊ አብዱልከሪም መንግሥቱ፥ ለወባ መራቢያነት ምቹ ሁኔታዎች በመኖራቸው በተቀናጀ መልኩ የመከላከል ስራው ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል። በመሆኑም ከባለፈው ዓመት ጀምሮ "የአርብ እጆች የወባ በሽታን ይገታሉ" በሚል መሪ ሃሳብ እየተተገበረ ያለው የወባ መከላከል ንቅናቄ በውጤታማነት መቀጠሉን ገልጸዋል። የአማራ ክልል የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በላይ በዛብህ፥በክልሉ የወባ ስርጭት በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የመከላከል ስራ በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉን ተናግረዋል። በዚህም መሰረት ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማዳፈን፣ አጎበርን በአግባቡ የመጠቀምና መሰል የመከላከል ስራዎች እንዲሁም የሕክምና ተደራሽነትን የማከናወን ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር)፥የወባ በሽታን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ በመስጠት ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ሚናውን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። በክልሉ በተለይም ለወባ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የግንዛቤ ፈጠራ እና የመከላከል ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።
በሆስፒታሉ ፈጣንና ቀልጣፋ የህክምና አገልግሎት እያገኘን ነው-ተገልጋዮች
Oct 15, 2025 144
አምቦ፤ ጥቅምት 5/2018(ኢዜአ)፡-የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ፈጣንና ቀልጣፋ የህክምና አገልግሎት እያገኙ መሆኑን የሆስፒታሉ ተገልጋዮች ተናገሩ። ከሆስፒታሉ ታካሚዎች መካከል አቶ ደሞዜ ሆርዶፋ፣ ከዚህ ቀደም በሆስፒታሉ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ረጅም ወረፋ መጠበቅና እንግልት ነበር ብለዋል። በተጨማሪም የመድሃኒት አቅርቦት በሆስፒታሉ ውስጥ በቀላሉ ስለማይገኝ መድሃኒት ለመግዛት ለተጨማሪ ወጪ ሲዳረጉ መቆየታቸውን ተናግረዋል። አሁን ላይ የሆስፒታሉ አሰራር ተሻሽሎ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ጠቅሰው የተጀመረው መልካም ስራ እንዲጠናከር ጠይቀዋል። ለእርግዝና ክትትል ወደ ሆስፒታሉ የመጡት ወይዘሮ ገማዴ ጌታሁን፣ ለክትትል ወደ ሆስፒታሉ በሚመላለሱበት ወቅት የተሻለ የህክምና አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም የታካሚ ካርድ ተፈልጎ ስለማይገኝ ለብዙ እንግልት እና ምልልስ ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰው በዚህ ወቅት በአጭር ጊዜ ውስጥ ካርድ አውጥተው የህክምና አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል። ልጃቸውን ለማሳከም ወደ ሆስፒታሉ የመጡት አቶ ተረፈ ጋዲሳ በበኩላቸው በሆስፒታሉ የነበረው አሰራር ተለውጦ በቴክኖሎጂ በመደገፉ የተሻለ አገልግሎት ከማግኘትም በተጨማሪ ጊዜያቸውንም እንደቆጠበላቸው አንስተዋል። የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና አገልግሎት ዳይሬክተር ዶክተር ኪሱ መስቀሌ ሆስፒታሉ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥን የሚያሻሽሉ ስራዎች ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል። በተለይም ከካርድ አሰጣጥ ጀምሮ ታካሚዎች ፈጥነው አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት መጀመሩንም ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም በሆስፒታሉ ያልነበሩ የህክምና ቁሳቁሶችን ማሟላት በመቻሉም ታካሚዎች ወደ አዲስ አበባና ሌሎች አካባቢዎች የተሻለ ህክምና ፍለጋ ያደርጉ የነበረውን ጉዞ፣ ወጪና እንግልት ማስቀረት መቻሉንም አንስተዋል። ከዚህ ጎን ለጎን የሆስፒታሉ ባለሙያዎች ርህራሄን እና ትዕግስትን ተላብሰው ታካሚዎችን ማገልገል እንዲችሉ ተደርጓል ብለዋል። የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶክተር ጎንፋ ሞቲ በበኩላቸው ሆስፒታሉን በተሻለ መልኩ በግብዓት የማሟላት ስራ በተከታታይ ሲከናውን መቆየቱን አንስተዋል። በዚህም የአካባቢው ማህበረሰብ ለተጨማሪ ወጪና እንግልት ሳይዳረግ በአቅራቢያው የተሻለ ህክምና ማግኘት መቻሉን አውስተዋል። በሆስፒታሉ በተከናወነ የማስፋፊያ ስራ የአእምሮ፣ የካንሰር፣ የኩላሊት እና ሌሎች የህክምና አገልግሎቶች በተሻለ መልኩ እየተሰጡ መሆኑን ገልጸዋል።
አዲስ የሲኒማ ኮምፕሌክስ ለሲኒማው ዘርፍ ጥራት መሻሻልና ዕድገት ወሳኝ ምዕራፍ የሚከፍት ነው
Oct 15, 2025 89
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):- አዲስ የሲኒማ ኮምፕሌክስ ለሲኒማው ዘርፍ ጥራት መሻሻልና ዕድገት ወሳኝ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሲሉ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ገለፁ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ24 ሺህ ካሬ ላይ ያስገነባውን አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ትናንት ሥራ አስጀምሯል። ኮምፕሌክሱ እጅግ ዘመናዊና ወቅቱ የደረሰበት ቴክኖሎጂ የተሟላለት፣ ባለ 15 ወለል ሲሆን፤ ባለ አራት ወለል የተሽከርካሪ ማቆሚያ የያዘ ነው። በተጨማሪም 592 ህፃናትና 887 አዋቂዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት የሲኒማ አዳራሾች ያለው ሲሆን፤ በቂ የሆነ የድምፅ ማስተላለፊያ ሲስተም፣ ዘመናዊ የመብራት ስርጭት፣ የአየር መቆጣጠሪያ መሳሪያዎች የተሟላለት ነው። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ አርቲስቶች መካከል አርቲስት አለልኝ መኳንንት ፅጌ እንደተናገረው፤ መንግስት ኪነ ጥበብ ለሀገር እድገት ያለውን አበርክቶ በመገንዘብ እያከናወነ ያለው ተግባር አበረታች ነው። ይህ እጅግ ዘመናዊ ሲኒማ ኮምፕሌክስ መገንባቱ ለኪነ ጥበብ ባለሙያዎችና ቤተሰቦች ትልቅ የምስራች መሆኑን ገልጿል። በሲኒማ ኮምፕሌክሱ ውስጥ ህጻናትን ታሳቢ ያደረጉ መሰረተ ልማቶች መካተታቸው ብቁ የሆኑ የጥበብ ባለሙያዎችን ለማፍራት የሚያስችል ነው ሲል ተናግሯል። አዲሱ የሲኒማ ኮምፕሌክስ የኪነ ጥበብ ዘርፉን ለማነቃቃት አይተኬ ሚና እንደሚጫወትም ተናግሯል። አርቲስት ቤዛነሽ አያሌው በበኩሏ፤ አዲሱ ሲኒማ ኮምፕሌክስ በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ምቾት እና ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ሆኖ በማግኘቷ አድናቆቷን ገልጻለች። ኮምፕሌክሱ ለየት ባለ መልኩ የተገነባ መሆኑን ጠቁማ፤ የተሻሉ ስራዎችን ለኪነ ጥበብ ቤተሰቦች ለማቅረብና ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ባለሙያዎች ለማፍራት ያስችላል ብላለች። ተዋናይ ደሳለኝ አሳምነው በበኩሉ በሲኒማው ውስጥ የተካተቱት መሰረተ ልማቶች መጪውን ትውልድ ታሳቢ በማድረግ የተሰሩ በመሆናቸው ብቁ የሆኑ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችን ለማፍራት ይረዳል ብሏል። የቴአትርና ኪነ ጥበብ አሰልጣኝ ሸዊት አብርሃም ደግሞ፤ የሲኒማ ኮምፕሌክስ መገንባቱ መንግስት ለዘርፉ እድገት የሰጠውን ትኩረት እንደሚያረጋግጥ ተናግሯል። አዲሱ የሲኒማ ኮምፕሌክስ መገንባቱ በኪነ ጥበብ ቤተሰብ ዘንድ መነቃቃትን እንደሚፈጥርም እንዲሁ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎችም ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በዓይነቱ የመጀመሪያ እና እጅግ ዘመናዊ የሆነውን የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስን አስመርቆ ስራ ማስጀመሩ ይታወሳል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርጥ የዘላቂ የደን ልማት አለም አቀፍ እውቅና አገኘ
Oct 15, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርጥ የዘላቂ የደን ልማት አያያዝና አጠቃቀም በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) እውቅና አግኝቷል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ እውቅናውን ያገኘችው በጣሊያን ሮም እየተካሄደ ባለው የዓለም ምግብ ጉባዔ ላይ ነው። የዓለም የምግብ ጉባኤውም የምስረታ በዓሉ አካል ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ ሀገራት ተሳትፈዋል። ድርጅቱ ለኢትዮጵያ "በአረንጓዴ አሻራ ዘላቂ የደን ልማት አያያዝና አጠቃቀም" በሚል ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና የሰጠ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግስትን ወክለው የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ሽልማቱን ተቀብለዋል። የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በመርሃ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ፋኦ ርሃብን ለማጥፋት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስና የአካባቢ ጥበቃን ለማጠናከር ላለፉት 80 ዓመታት የላቀ አሻራ ማሳረፉን አንስተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ዛሬ በምርጥ የዘላቂ የደን ልማትና ጥበቃ ምሳሌነት እውቅና በማግኘቱ ኮርተናል ብለዋል። በመርሃ ግብሩ በብዙ ቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋንን ከ17 ነጥብ 2 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደጉን ተናግረዋል። ይህ በመሪ ግልፅ ራዕይና በህዝብ ጠንካራ ተሳትፎ የተሳካና ተስፋችንን ያለመለመ ስኬት ነው ያሉት ሚኒስትሯ፥ ይህንን ተጨባጭ ሥራ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እንዲጎበኙና በዓይን አይተው እንዲመሰክሩም ጋብዘዋል። ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ጋር ላለው ለረጅም ጊዜ የጸና አጋርነት ያመሰገኑት ሚኒስትሯ በጋራ ጥረታችን ችግኞችን እየተከልን የተሻለ ነገን ለልጆቻችን መገንባት ጀምረናል ብለዋል። የዓለም የምግብና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ) ከዚህ ቀደም በምግብ ዋስትና፣ በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦትና በስንዴ ምርት የላቀ አፈጻጸም ላሳዩት ቁርጠኝነት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሸለሙ ይታወሳል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዓለም የምግብና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ) 80ኛ የምስረታ ዓመት የድርጅቱን ያለፉት ዓመታት ስራዎች በሚዳስሱ እንዲሁም ቀጣይ ራዕዩን በሚገልጡ ዝግጅቶች እያከበረ ይገኛል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ለልማት ሥራዎች መፋጠን ተሳትፏችንን እናጠናክራለን - ባለሀብቶች
Oct 15, 2025 52
ጋምቤላ፤ ጥቅምት 5/ 2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለተጀመሩ የልማት ሥራዎች መፋጠን ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በተለያዩ የንግድና የኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩ ባለሃብቶች ገለጹ። በክልሉ የልማትና የንግድ እንቅስቃሴ ዙሪያ በጋምቤላ ከተማ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ተጠናቋል ። ከውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች መካከል በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት ባለሃብት አቶ ኡሞድ ኡገር እንደገለጹት በክልሉ ለተጀመሩ የኮሪደርና ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ የልማት ሥራዎች መሳካት የበኩላቸውን ተሳትፎ ለማድረግ ዝግጁ ናቸው። የአቅመ ደካማ ቤቶችን መገንባትን ጨምሮ በሌሎች የልማት ስራዎች ሲሳተፉ መቆየታቸውን የገለጹት ደግሞ በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት አቶ ንጉስ በራ ናቸው። በቀጣይም በክልሉ በተጀመሩ የኮሪደርና ሌሎች ስራዎች ተሳትፏቸውን ይበልጥ አጠናከረው ለመቀጠል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሌላዋ በሆቴል ስራ የተሰማሩት ወይዘሮ አምሳለ ገብረወልድ በሰጡት አስተያየት የንግዱ ማህበረሰብ በክልሉ የሰላምና የልማት ስራዎች ተሳትፏችንን እናጠናክራለን ብለዋል ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንዳሉት ለክልሉ ልማትና እድገት መፋጠን የባለሀብቱ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ። የንግዱ ማህበረሰብና ባለሀብቱ በልማት ስራዎች ተሳትፏቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ሪፎርም እና የልማት ስራ ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል-የባንኩ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ
Oct 15, 2025 106
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ሪፎርም እና የልማት ስራ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የባንኩ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ አስታወቁ። የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) አመታዊ ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ነው። በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በዓመታዊው ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። ልዑካን ቡድኑ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ያካተተ ነው። የመንግስት ከፍተኛ ልዑካን ቡድኑ ከዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ ጋር ተወያይቷል። የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ልማት ያደረገውን የረጅም ጊዜ እና ዘርፈ ብዙ ድጋፍ አድንቀዋል። ባንኩ ለኢትዮጵያ ቁልፍ የኢኮኖሚ ዘርፎች ያለው አጠቃላይ የፋይናንስ ማዕቀፍ ከ16 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሻገሩን አመልክተዋል። ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ጠንካራ የኢኮኖሚ እድገት፣የወጪ ንግድ እና ሬሚታንስ እድገት፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማደግ እና የዋጋ ንረት መቀነስ በሪፎርሙ ከተገኙ ውጤቶች መካከል እንደሚጠቀሱ አንስተዋል። በውይይቱ አቶ አሕመድ፥ የኢትዮጵያ መንግስት ቁልፍ የልማት የትኩረት መስኮችን አንስተዋል። የግብርና ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን፣ የሰው ሀብት ልማት ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የግል የፋይናንስ ሀብት ማሰባሰብ፣ አማራጭ የፋይናንስ መፍትሄዎች መፈለግ እንዲሁም ቀጣናዊ እንዲሁም የባለብዙ ወገን ትብብርን ማጠናከር ሚኒስትሩ ያነሷቸው የትኩረት አጀንዳዎች ናቸው። የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ፥ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት እያደረገቻቸው ያሉ ጠንካራ እና ታሪካዊ የኢኮኖሚ ሪፎርሞችን አድንቀዋል። ፕሬዝዳንቱ የኢትዮጵያን ሀገራዊ ምክክር ያደነቁ ሲሆን ሂደቱ ማህበራዊ ትስስርን በማጠናከር ኢትዮጵያ አቅሟን ተጠቅማ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ እድገት እንድታስመዘግብ የሚያስችል ቁልፍ እርምጃ እንደሆነ ተናግረዋል። የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ የልማት ጉዞ፣ የሪፎርም አጀንዳ እና የልማት የትኩረት መስኮችን ለመደገፍ ቁርጠኛ ነው ብለዋል። የማክሮ ኢኮኖሚ ሂደቱ ዘላቂ የሆነ የልማት ውጤት እንዲያመጣ ድጋፉን እንደሚያደርግ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
የመሰረተ ልማት ስራዎች ተጠብቀው የዜጎች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ህግ የማስከበር ስራችንን እናጠናክራለን - ፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት
Oct 15, 2025 95
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፡-በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ የመሰረተ ልማት ስራዎች ተጠብቀው የዜጎች ተጠቃሚነትን የበለጠ ለማረጋገጥ ህግ የማስከበር ተግባራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት ገለጹ። የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት ከእንጦጦ ፓርክ እስከ አቃቂ ቃሊቲ ድረስ የተሰሩ የኮሪደር ልማት እና ልዩ ልዩ መሰረተ ልማቶች ስራዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት እንደገለጹት፤ በከተማዋ በተገነቡ መሰረተ ልማት ስራዎች እጅግ ተደንቀዋል። በፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ጤና አገልግሎት ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አብደላ አደላ፤ አዲስ አበባን ጨምሮ በመላው አገሪቷ እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ስራዎች የሰላም ፍሬ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። የአገር ልማት የሚረጋገጠው ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ሲሰፍን ብቻ መሆኑን ጠቁመው፤ "ሰላምና ልማት የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው" ብለዋል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ሰላምን የማስጠበቅና ልማትን እንዲፋጠን የማድረግ ተግባርን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው የተናገሩት፡፡ በፌዴራል ፖሊስ ሆስፒታል የግዥ ሃላፊ ኮማንደር ባዬ ሽፈራው በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የከተማዋ ውበት፣ መሰረተ ልማቶች አገሪቷ ፈጣን እድገት ውስጥ መሆኗን አመላካቾች ናቸው። ፖሊስ የልማት አደናቃፊ እና የፀረ ሰላም ሃይሎችን እኩይ ተግባር እያከሸፈ መምጣቱን አውስተው፤ ይህን ተግባሩን ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ በፌዴራል ፖሊስ የልዩ ፀረ ሽብር ኮማንዶ አባል ዋና ኢንስፔክተር አየለ አሸናፊ፤ በዛሬው ጉብኝታችን አገራችን እየተጓዘችበት ያለውን ከፍታ በተግባር ያየነበትና ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ረዳት ኢንስፔክተር ማርታ ወረቁ በበኩላቸው፤ የህዝብንና የአገርን ሰላም ለማረጋገጥ የሚከፈለው ዋጋ ለዚህ ዓይነት የልማት ስራዎች አብቅቶናል ብለዋል። በፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ተቋም ጥበቃ መምሪያ የሬጅመንት አዛዥ ኮሎኔል ማቲዮስ ሸጋው እንደገለጹት፤ ፖሊስ ህዝብና መንግስት በሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች የራሱን አሻራ የማኖር ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በአፋር ክልል የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ የዲጂታል አገልግሎት ተዘርግቷል
Oct 15, 2025 66
ሰመራ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ የዲጂታል አገልግሎት መዘርጋቱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ የጭፍራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የዲጂታላይዝ አገልግሎት ዛሬ ወደ ስራ ገብቷል። በአገልግሎቱ ማስጀመሪያ ስነ ስርአት ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ኀላፊ አቶ ያሲን ሃቢብ እንደተናገሩት በክልሉ የጤና አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነት በማረጋገጥ የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ እየተሰራ ነው። የጤና አገልግሎቱን ጥራትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ የዲጂታል መረጃ አያያዝንና የሰው ሀይል አቅም ግንባታ ላይ መሰራቱን አክለዋል። ይህም የጤናውን ዘርፍ በተጠናከረ መረጃ በመደገፍ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት አስተማማኝና ፈጣን ለማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል። ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረው የጭፍራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትም የዚሁ ጥረት አካል ነው ብለዋል። ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነው ይህ አገልግሎት የተደራጀ የጤና መረጃን በቀላሉ ለህክምና ተግባሩ ለማዋል እንደሚያግዝ ተናግረዋል። አገልግሎቱን በቀጣይም ወደ ሌሎች ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች የማስቀጠል ተግባር እንደሚከናወን አመላክተዋል። የጭፍራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አሊ አርባ በበኩላቸው በቴክኖሎጂ የተደገፈው የሆስፒታሉ አገልግሎት መረጃን በአግባቡ በማደራጀት ግልጽነትን ከመፍጠር ባለፈ ወረፋን የሚያስቀር መሆኑን ተናግረዋል። የጭፍራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ አሚን ኡመር እንዳሉት በይፋ የተጀመረው አገልግሎት ለህክምና አሰጣጥ መቀላጠፍ፣ ለጥናትና ምርምር የተደራጁ መረጃዎችን ለማግኘት እንደ መረጃ ቋት ሆኖ ያገለግላል። በተለይም የህክምና አገልግሎትን ለማቀላጠፍ መረጃን በቀላሉ ለህክምናው ባለሞያ ተደራሽ በማድረግ ታካሚው ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችል ነው ብለዋል። በጤናው ዘርፍ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ጥራት ያለውና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ተጨማሪ እቅም እንደሚሆን ተናግረዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ወቅቱን የጠበቀና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የዲጂታል ስርዓት አስጀመረ
Oct 15, 2025 90
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቋማዊ አሰራሩን በማዘመን ወቅቱን የጠበቀና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የዲጂታል ስርዓትን ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያበለጸገውን ዲጂታል የሰነድና ማህደር አስተዳደርና ወረቀት አልባ የአሰራር ስርዓትን (record management and smart paperless office) ዛሬ ይፋ አድርጓል። ሚኒስቴሩ በወረቀት አልባ ስማርት አሰራርና የዲጂታል የሰነድ ልውውጥና አያያዝ ስርዓት ላይ ያተኮረ ስልጠና መስጠት ጀምሯል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ሚኒስቴሩ አንጋፋነቱን የሚመጥን በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ የአሰራር ሥርዓት አልነበረውም፡፡ አሁን ላይ የተቋማዊ ሪፎርሙ አካል የሆነ የዲጂታል አሰራር ትግበራ መጀመሩን ገልጸው፥ ለዚህም ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ዲጂታል ስርዓት ማልማቱን ገልጸዋል፡፡ የሰነድና ማህደር አስተዳደር ስርዓቱ በሚኒስቴሩ ከመዝገብ አያያዝ እስከ ሚሲዮኖች የመረጃ ልውውጥ ድረስ የነበረውን የወረቀት አሰራር በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ የአገልግሎት ስርዓት መፍጠር ያስችላል ብለዋል፡፡ ስልጠናውም በዲጂታል የሰነድ አስተዳደር፣ በውስጥ እና በውጪ ግንኙነት እና በደብዳቤ ልውውጥ እንዲሁም በተቀላጠፈ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የጋራ አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። ወቅቱን የዋጀ ስርዓት ዘመናዊ የሰነድ አያያዝ ሥርዓት ከመፍጠር ባለፈ ጊዜንና ወጪን እንደሚቆጥብ ጠቁመዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወሻዎች፣ ጥናቶችና ታሪካዊ ፋይዳ ያላቸው ትልልቅ ሰነዶች የመነጩበት ተቋም መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ የሶፍትዌር ስርዓቱ የተቋሙን ተሞክሮዎችና ታሪኮች በዘመናዊ መንገድ ለመሰነድ የጎላ አበርክቶ እንዳለው አንስተዋል፡፡ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት ልምድና አገልግሎት ለዲፕሎማቶች ለማሸጋገር የማይተካ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመረጃ ሀብትና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ጀነራል ዳንኤል ዘገዬ በበኩላቸው፤ ዲጂታል ስርዓቱ የውስጥ አሰራርና የመረጃ ልውውጦችን ከወረቀት ነጻ በማድረግ በኤሌክትሮኒክ ስርዓት መሰነድ ያስችላል ብለዋል፡፡ ከብሄራዊ ቤተመጻህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ወደ ዲጂታል ስርዓት የሚገቡ ሰነዶችን የመለየትና ቦታ የማስያዝ ሥራዎች መከናወናቸውንም ገልጸዋል፡፡ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተሰንደው መያዛቸው መረጃዎችን በቀላሉ ለውሳኔ አሰጣጥ፣ ለጥናትና ምርምር ግብዓት ጥቅም ላይ ለማዋል ያግዛል ብለዋል፡፡ የአሰራር ስርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ ለተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች መሰጠት የጀመረው ስልጠና ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሳይበር ደህንነት ያገኘቻቸውን ውጤቶች በዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መድረክ ላይ አቀረበች
Oct 15, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሳይበር ደህንነት ያገኘቻቸውን ውጤቶች በዱባይ እየተካሄደ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መድረክ ላይ አቅርባለች። 45ኛው የገልፍ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) በዓለም የንግድ ከተማ በሆነችው ዱባይ እየተካሄደ ይገኛል። ይህ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች፣ የመንግስት ተቋማት፣ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ኢኖቬተሮች እና ተመራማሪዎችን በአንድ መድረክ ያገናኘ የ2025 ጂአይቴክስ መድረክ በተለይ በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የሳይበር ደህንነት ላይ ትኩረት ያደረጉ ውይይቶችም እየተደረጉበት ነው፡ ፡ ዛሬ በተካሄደው እና ትኩረቱን የመንግስትና የግል ተቋማት ትብብር ላይ ባደረገው ውይይት ኢትዮጵያም ተሞክሮዋን አካፍላለች። ከግሪክ፣ ኦማን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬት የተሳተፉበት የዘርፉ ተወካዮች ጋር ተጋብዘው ንግግር ያደረጉት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዳንኤል ጉታ ባለፉት ጊዜያት ኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ያደረገቻቸውን ጥረቶች አስረድተዋል። አቶ ዳንኤል በማብራሪያቸው ባለፉት አምስት ዓመታት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በሚል የሀገሪቱን የዲጂታል ዘርፍ ለማሳደግ ሰፊ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች እንደተከናወኑ ገልጸዋል። አሁን ላይ በኢትዮጵያ ከ53 ሚሊዮን በላይ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች እንዳሉ ጠቁመው፤ የዘርፉ እድገት ዜጎች የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አንስተዋል። አቶ ዳንኤል በማብራሪያቸው የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘርፍ በፍጥነት እያደገ ከመሆኑ ጋር በተገናኘ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት መንግስት አዳዲስ ፖሊሲዎችንና አሰራሮችን በፍጥነት ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝም አብራርተዋል። በተለይ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ የሚሰሩበት ህብር የተሰኘ ቴክኖሎጂ በመፍጠር ወደ ስራ ለማስገባት እየተደረገ ያለውን ጥረት አስረድተዋል። ህብር በሳይበር ደህንነት ላይ የሚሰሩ ተቋማት፣ ግለሰቦች፣ የሳይበር ደህንነት አገልግሎት የሚፈልጉ ተቋማት እንዲሁም የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በጋራ እና በትብብር እንዲሰሩ የሚያስችላቸው ነው። በተጨማሪም የሳይበር ደህንነት ጥበቃ የሚል አዲስ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ መንግስት፣ የግል ድርጅቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በትብብር እና በቅንጅት ሊሰሩ የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑንም አቶ ዳንኤል ገልጸዋል። በቅርቡ የተሻሻለው የሳይበር ደህንነት ፖሊሲ አሁን እየመጡ ያሉ ስጋቶችን ለመከላከል ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም አመልክተዋል። የሀገሪቱ የዲጂታል 2030 ፖሊሲ ለሳይበር ደህንነት ልዩ ትኩረት የሰጠ መሆኑንም አቶ ዳንኤል በፖናል ውይይቱ ላይ ተናግረዋል። ከመድረኩ በኋላ ከPulse Of Africa ሚዲያ ጋር ቆይታ ያደረጉት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዳንኤል ጉታ ኢትዮጵያ በጂአይቴክስ ላይ መሳተፏ ሀገሪቷ በተለይ በቴክኖሎጂ፣ በሳይበር ደህንነት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ስማርት ሲቲ እና ሌሎች ዘርፎች ላይ እየሰራች ያለውን ውጤታማ ስራ ለማሳደግ ትልቅ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በ2025 ጂአይቴክስ ዱባይ ከ180 ሀገራት የተወጣጡ ከ6 ሺህ 500 በላይ አቅራቢዎች፣ ከ1 ሺህ 800 በላይ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች እና ከ1 ሺህ 200 በላይ ባለሀብቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ። ከጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ እየተካሄደ በሚገኘው አውደ ርዕይ በተለይ ከሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ጋር የተገናኙ ፈጠራዎች እና አገልግሎቶች በስፋት እየተዋወቁ ይገኛል። በተጨማሪም የጤና እና ባዮ ቴክኖሎጂዎች፣ ኮሙኒኬሽን፣ ሮቦቲክስ፣ የቀጣዩ ትውልድ ቴክኖሎጂዎች እና ሌሎች በርካታ ፈጠራዎች ለእይታ መቅረባቸውን የPulse Of Africa ሚዲያ መረጃ ያመለክታል።
ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ የድሮን ቴክኖሎጂ ምርቶችን ማምረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 14, 2025 196
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ የድሮን ቴክኖሎጂ ምርቶችን ማምረቱን አጠናክሮ መቀጠሉን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በሀገር ውስጥ ማምረት የጀመራቸውን ድሮኖች ምርት በማስፋት የድሮን ቴክኖሎጂን በምርምር እና ሥርፀት ለማሳደግ እንዲሁም ተግባራዊ ተሞክሮን ለማዳበር የሚያግዘውን ትብብር ለመፍጠር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከኢፌዴሪ አየር ኃይል፣ ከመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንደስትሪ ግሩፕ፣ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈራረሙን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ ገልጸዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ በመርሐ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት፥ ብሔራዊ ጥቅምን ከማስከበር እንዲሁም ካለው የላቀ ኢኮኖሚያዊና ስትራቴጂያዊ ፋይዳ አንጻር የድሮን ቴክኖሎጂን በራስ አቅም ማልማት ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ ነው፡፡ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባትም የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ተመርቆ ስራ የጀመረው ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ ለደኅንነት፣ ለመረጃ ስምሪት፣ለሲቪልና ለወታደራዊ አገልግሎቶች የሚውሉ ድሮኖች ምርትን አጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። የድሮን ቴክኖሎጂ በፈጣን ዕድገት ላይ የሚገኝ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሲሳይ፤ እንደ ሀገር ብሔራዊ ጥቅምን ከማስጠበቅ፣ ኢኮኖሚያዊ እድገትን ከማሳለጥ እንዲሁም ወደፊት የሚቃጡ ጥቃቶችን ውጤት ከመወሰን አንፃር ያለውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ በመመዘን በድሮን ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ ገልጿል፡፡ በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆንና በሀገር ውስጥ የተፈጠረውን የድሮን ቴክኖሎጂ ዐቅም ለማጎልበት የአንድ ተቋም እንቅስቃሴ ብቻ በቂ ባለመሆኑ ከአምስቱ ተቋማት ጋር በትብበር እና አጋርነት ለመስራት ስምምነቱ ማስፈለጉን የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ አብራርተዋል፡፡ ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ የሚያመርታቸውን ድሮኖች በዓይነትና በጥራት ለማሳደግ የድሮን ቴክኖሎጂ የሚጠቀማቸውን ስማርት ሴንሰሮች በተመለከተ ከአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አስተዳደር፤ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዘርፉን ምርምር ውጤቶችና የሰለጠነ የሰው ኃይል፤ በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንደስትሪ በኩል ለውጊያ የሚውሉ ድሮኖች የሚታጠቋቸው ጦር መሳሪያዎች ምርትን፤ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የካበተ የአቪዬሽን ዘርፍ ተሞክሮ እንዲሁም ከኢፌዴሪ አየር ኃይል በኩል ተግባራዊ ልምምድ ለመቅሰም ታልሞ የትብበር ስምምነቱ መፈረሙ ተመልክቷል፡፡ ከመግባቢያ ሰነድ ፊርማው በኋላ የስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪና የድሮን ምርቶቹ የተጎበኙ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በዘርፉ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማረጋገጥ እና በሀገር ውስጥ ያሉትን የተለያዩ ተቋማት እና ዩኒቨርሲቲዎች ዕውቀት፣ ልምድና ሀብት በመደመር ውጤታማነትን ለማረጋገጥ በትብብር ለመስራት የወሰደው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘርፉ በሚያደርጋቸው ምርምር እና ልማት እንዲሁም የሰው ኃይልን በማሰልጠን ከስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ ያለውን ተሞክሮ ማካፈል ብቻ ሳይሆን ወደፊት በስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ የሚመረቱ ድሮኖችን መጠቀም የሚችልበት ዕድሎች መኖራቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በዓለማችን ሀገራት ውጥረት ውስጥ በገቡ ጊዜ ሉዓላዊነታቸውን ለማስከበር በሚያካሄዷቸው ማናቸውም ኦፕሬሽኖች ላይ የድሮን ቴክኖሎጂ ሚናው እያደገ መምጣቱን የጠቀሱት የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንደስትሪ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታቸው ሃይለማርያም፤ የሀገራችንን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዘርፉን በራስ አቅም በተገቢው መንገድ ለመጠቀም በትብብር ለመስራት አጋጣሚው ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ አነስተኛ እና መካከለኛ ድሮኖችን በማምረት ስራውን የጀመረ ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪ እ.አ.አ በ2030 ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸው ትላልቅ ድሮኖችን በማምረት ለዓለም ገበያ የማቅረብ ራዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደምም ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ስምምነት ፈጽሟል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በቡርኪናፋሶ አቻው ተሸነፈ
Oct 13, 2025 238
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ከቡርኪናፋሶ ጋር ባደረገው ጨዋታ 3 ለ 1 ተሸንፏል። ማምሻውን በኦገስት 4 ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ተቀይሮ የገባው ፒዬር ላንዲ ካቦሬ በ64ኛው፣ በ82ኛው እና በ96 ደቂቃ የማሸነፊያ ግቦቹን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። ቢኒያም አይተን በ84ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቱን ተከትሎ በምድብ አንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ በዘጠኝ ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ቡርኪናፋሶ በ21 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ምርጥ ሁለተኛ ሆኖ በጥሎ ለማለፍ ከሚሳተፉ አራት የአፍሪካ ሀገራት አንዷ የመሆን እድሏን አስፍታለች። በዚሁ ምድብ ማምሻውን በተደረገው ጨዋታ ግብጽ ጊኒ ቢሳውን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ለዓለም ዋንጫ ያለፈው ቡድኑ በ26 ነጥብ ምድቡን በመሪነት አጠናቋል። በዚሁ ምድብ በተደረገው ጨዋታ ሴራሊዮን ጅቡቲን 2 ለ 1 አሸንፋለች።
ኢትዮጵያ የዓለም ዋንጫ የመጨረሻ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዋን ከቡርኪናፋሶ ጋር ዛሬ ታደርጋለች
Oct 12, 2025 185
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ዛሬ ከቡርኪናፋሶ ጋር ትጫወታለች። የሀገራቱ ጨዋታ በኦገስት 4 ስታዲየም ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ ይደረጋል። በምድብ አንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ በዘጠኝ ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በፊት ከጊኒ ቢሳው ጋር ባደረገው የማጣሪያ መርሃ ግብር 1 ለ 0 በማሸነፍ በምድቡ ሁለተኛ ድሉን ማስመዝገቡ ይታወቃል። በብራማ ትራኦሬ የሚሰለጥነው የቡርኪናፋሶ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በፊት ከሴራሊዮን ጋር ባደረገው ጨዋታ 1 ለ 0 አሸንፏል። ቡድኑ ነጥቡን ወደ 18 ከፍ በማድረግ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሁለቱ ሀገራት በዚሁ ምድብ ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ ቡርኪናፋሶ 3 ለ 0 ማሸነፏ የሚታወስ ነው። ሀገራቱ ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው አምስት የእርስ በእርስ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ አንድ ጊዜ ስታሸንፍ ቡርኪናፋሶ ሶስት ጊዜ ድል ቀንቷታል። አንድ ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። በጨዋታዎቹ ቡርኪናፋሶ 12 ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ኢትዮጵያ ሶስት ግቦችን አስቆጥራለች። ከዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ ለሆነው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የዛሬው ጨዋታ የማጣሪያ ጉዞውን በድል ለመደምደም ያስችለዋል። ቡርኪናፋሶ ማሸነፍ ከቻለች ለዓለም ዋንጫው ለማለፍ በሚደረገው የጥሎ ማለፍ ውድድር ለመሳተፍ የሚያስችላትን እድል ታሰፋለች። በዚሁ ምድብ የምትገኘው ግብጽ በ23 ነጥብ ለዓለም ዋንጫ በቀጥታ ማለፏ የሚታወስ ነው። በምድብ አንድ ግብጽ ከጊኒ ቢሳው፣ ጅቡቲ ከሴራሊዮን ዛሬ በተመሳሳይ ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በድሬዳዋ ከተማ ሊደረጉ የነበሩ የሊጉ የመክፈቻ ጨዋታዎች ወደ ሃዋሳ ተዘዋውረዋል
Oct 11, 2025 233
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በድሬዳዋ ሊደረጉ የነበሩ የመክፈቻ ጨዋታዎች ወደ ሃዋሳ መዘዋወራቸውን የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታወቀ። የሊጉ የመጀመሪያ ዘጠኝ ሳምንታት ውድድር በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ እንደሚደረግ መገለጹ ይታወቃል። ይሁንና በአሁኑ ወቅት ድሬዳዋ ከተማ ውድድሩን ለማስተናገድ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠ በመሆኑና ዝግጁ አለመሆኑን በመግለጹ ድሬዳዋ ላይ ሊደረጉ የነበሩ የመክፈቻ ሳምንታት ጨዋታዎች ወደ ሃዋሳ ከተማ መዞሩን ማህበሩ ገልጿል። የተስተካከለውን መርሃ ግብር በቅርቡ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል። 20 ክለቦች በሁለት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርትን በማስፋት ረገድ በአፍሪካ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች ነው
Oct 15, 2025 98
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):-ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም ለአረንጓዴ ትራንስፖርት መስፋፋት በአፍሪካ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። "በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የትራንስፖርት ስርዓትን ማረጋገጥ" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መካሄድ የጀመረው የ2025 የአፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ሳምንት የመክፈቻ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡ መድረኩ ለአህጉሪቱ ዘላቂ ትራንስፖርት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማስፋፋት ለአየር ንብረት የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት ቁልፍ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ፣ በአከባቢ ጥበቃ ብሎም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማስፋፋት አረንጓዴ የትራንስፖርት ስርዓትና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ እየገነባች እንደምትገኝም ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ አበረታች የፖሊሲ ማዕቀፍ በማዘጋጀት የትራንስፖርት ምህዳሯን በመሠረታዊነት እየቀየረች መሆኑንም ጠቁመዋል። በጋራ አቅም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የማምረት፣ የኃይል መሙያ መሠረተ ልማትን ማስፋፋት እንዲሁም ቀጣናዊ የተቀናጁ የእሴት ሰንሰለቶችን መፍጠር እንደሚቻል አመልክተዋል። አፍሪካ ቴክኖሎጂዎችን በራሷ አቅም ለማልማት ትልቅ ትኩረት መስጠት እንዳለባት ጠቁመው፥ በትራንስፖርት ዘርፉ ዘላቂ ለውጥን ማምጣት የሚያስችል ፈጠራ ላይ የተመሰረተ የተሻለ ነገን ልንቀርጽ ይገባል ብለዋል። የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን፣ የሀገሪቱን የታዳሽ ኃይል አቅም መጠቀም የሚችል የትራንስፖርት ዘርፍ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ማስፋፋት የሰጠችው ከፍተኛ ትኩረት እውቅና እንደተሰጠው አመላካች መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስትራቴጂ በማጽደቅ ወደ ትግበራ ማስገባቷን ገልጸዋል፡፡ መንግሥት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ ባደረገው የቀረጥ ማበረታቻ ምክንያት በርካታ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እየገቡ መሆኑን አስታውቀዋል። ጉባዔው የአፍሪካ ሀገራትን የብሉ ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥበትም ተጠቁሟል፡፡
ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች ነው
Oct 13, 2025 202
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓትን ለማስፋት በፖሊሲ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደች መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ገለጹ፡፡ በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስተባባሪነት በአረንጓዴ ትራንስፖርትና በታዳሽ ኃይል ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች የአዳማ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተጎብኝቷል፡፡ በጉብኝቱ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን፣ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰንን ጨምሮ ከኢትዮጵያ እና ኬንያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ ኩባንያዎች ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴዔታ በርኦ ሀሰን በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የትራንስፖርት ዘርፉን ጨምሮ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ ባከናወነቻቸው ተግባራት በርካታ ለውጦችን አስመዝግባለች ብለዋል፡፡ ለዚህም በሕዳሴ ግድብ፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብርና በንፋስ ኃይል ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች ትልቅ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዘርፉን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅና ከአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ የጸዳ እንዲሆን ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል፡፡ መንግሥት ታዳሽ ኃይል የሚጠቀም የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍን እውን ለማድረግ ጠንካራ የፖሊሲ ድጋፍ ስለማድረጉ አንስተዋል። በዚህም በርካታ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በማንሳት፥ ባለሀብቶችም በዘርፉ ኢንቨስት እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና መንግስት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ስርዓት የተሰማሩ ተቋማትን እንደሚያበረታታ አረጋግጠዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ላይ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለዓለም ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ናቸው ብለዋል፡፡ በተለይ ደግሞ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ የወሰደው እርምጃ ይበል የሚባል ነው ብለዋል፡፡ ሀገራቸው ይህንን ተግባር እንደምትደግፍም አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ሳምንት ከነገ ጥቅምት 4 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 6 ቀን 2018 በአዲስ አበባ ይካሔዳል፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ የብዙሃን ትራንፖርት፣ ባቡር፣ ኮሪደር ልማት፣ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች እንዲሁም በፖሊሲ ረገድ እያከናወነች ያለችውን ተጨባጭ ሥራ እንደምታቀርብም ተገልጿል።
ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ተረፈ ምርቶችን ወደ ሐብት በመቀየር ውጤታማ እየሆኑ ነው
Oct 13, 2025 130
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ተረፈ ምርቶችን ወደ ሐብት በመቀየር ገቢ ከማመንጨት ባለፈ በአካባቢ ጥበቃ እና በስራ ዕድል ፈጠራ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ገለጹ። በኢትዮጵያ በቅርቡ ብሔራዊ የሰርኩላር ኢኮኖሚ ፍኖተ ካርታ ይፋ የተደረገ ሲሆን ቆሻሻን መልሶ መጠቀምን ማስፋፋት፣ ለአካባቢ ተስማሚ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት እና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ላይ የተመሠረቱ የሥራ ዕድሎችን ማስፋት ከዋና ዓላማዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የአካበቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ እንደተናገሩት ለፍኖተ ካርታው ውጤታማነት የግል ዘርፉ ተሳትፎ የጎላ ነው። ፍኖተ ካርታው ጽዱ ኢትዮጵያን ከማሳካት አንጻር የግሉ ዘርፍ ትልቁን ድርሻ እንዲወጣ የሚያስችል ነው ብለዋል። የግሉ ዘርፍ የሚያስፈልገውን የፋይናንስ፣ የቴክኖሎጂና ሌሎች ድጋፎች ያካተተ የተቀናጀ ስርዓት የሚዘረጋ መሆኑንም ተናግረዋል። ብሔራዊ የሰርኩላር ኢኮኖሚ ፍኖተ ካርታ ግቦችን ከማሳካት አንጻር ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ተረፈ ምርቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ለአካባቢ ተስማሚና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ምርቶችን በማምረት የጀመሩት ሥራ ምሳሌ ሆኖ የሚቀርብ ነው። ወጣት ሚካኤል ኃይሌ ጥቅም ላይ የዋሉ ወረቀቶችን በመሰብሰብና መልሶ በመጠቀም የተለያዩ ምርቶችን በማምረት ላይ እንደሚገኝ ይናገራል። ምርቶቹም ለተቋማት ማስታወቂያ፣ ለጌጣጌጥ፣ ለስጦታና ለሌሎች አገልግሎቶች እየዋሉ መሆኑን ጠቁሞ የቆሻሻ አሰባሰብ ሂደቱን ከማህበረሰቡ ጋር በማስተሳሰር የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልጿል፡፡ ከየተቋማቱ የሚጣሉ ወረቀቶችን ለሚሰበስቡ ለበርካታ የጽዳት ሠራተኞችና ሴቶች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸውም አስረድቷል። ወጣት ኢያሱ መዝገቡ የሙዝ ልጣጭን ከሌሎች ግብዓቶች ጋር በመጠቀም ለቤትና ቢሮ ቁሳቁሶች፣ ለጫማ እንዲሁም ለተለያዩ የቆዳ ምርቶች የሚውል አካባቢን የማይጎዳ ቀለም እያመረተ መሆኑን ገልፅዋል። የእንጨት ተረፈ ምርቶችን በመጠቀም በውስጡ የሚገኘውን መርዛማ ጋዝ በማውጣት ለጤና የማይጎዳ የከሰል ምርት እያመረተ እንደሚገኝ የተናገረው ደግሞ ወጣት ኢዮብ አለሙ ነው፡፡ ምርቱ ከእንጨት ተረፈ ምርት የሚመረት በመሆኑ የደን ጭፍጨፋን በመከላከል ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጿል። ይህም የሀገሪቱን የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር እና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሥራዎችን በመደገፍ ረገድ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት አመልክቷል። ወጣቶቹ እንዳሉትም በቀጣይም ምርቶቻቸውን በስፋት በማምረት የሥራ ዕድል ፈጠራን ይበልጥ ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ገልጸዋል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን በክረምት ወራት ለተተከሉ ችግኞች የሚደረገው እንክብካቤ ቀጥሏል
Oct 11, 2025 237
ጊምቢ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን በክረምት ወራት ለተተከሉ ችግኞች የሚደረገው እንክብካቤ መቀጠሉን የዞኑ የግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። የምዕራብ ወለጋ ዞን የግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፈይሳ ሀምቢሳ እንደገለጹት በዞኑ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተተክለዋል። ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች ውጤታማ እንዲሆኑ በዞኑ ነዋሪዎች የችግኝ እንክብካቤ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ወቅትም በተለይም ባለፈው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በተጠናከረ መልኩ እየተካሄደ ነው ብለዋል። በአጠቃላይ በዞኑ ባለፉት ዓመታት በተከናወነ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች አካባቢውን አረንጓዴ ከማልበስ ባለፈ ለግብርና ስራም እገዛ እያደረጉ መሆኑ ገልጸዋል። በችግኝ እንክብካቤው እየተሳተፉ ከሚገኙ መካከል ወይዘሮ ለሊሴ ብርሃኑ፣ በክረምት ወራት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን እየተንከባከቡ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በአካባቢያቸው በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተተከሉ ችግኞች ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ መሆኑን በመገንዘባቸው አሁንም በእንክብካቤው መጠንከራቸውን ጠቅሰዋል። አቶ ገረመው ነገራ በበኩላቸው የተተከሉ ችግኞች ለውጤት እንዲበቁ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ሁሉም በየአካባቢው ችግኞችን በመንከባከብ ለውጤት ማብቃት አለበት ያሉት ደግሞ አቶ ነጻነት አበበ ሲሆኑ ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች የተለያየ ጥቅም እየሰጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ
Oct 15, 2025 127
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር እና በአህጉሪቷ የማካካሻ ፍትህን ለማረጋገጥ በበለጠ ቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን በአፍሪካ ደረጃ ዛሬ በአህጉሪቷ መዲና አዲስ አበባ ዛሬ ይከበራል። “የገጠር ሴቶችን በማካካሻ ፍትህ አማካኝነት ማብቃት፤ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ስርዓተ ምግብን ማረጋገጥ” የቀኑ መሪ ሀሳብ ነው። በቀኑ አከባበር ላይ የአፍሪካ ህብረት አመራሮች፣ የመንግስታት ተወካዮች፣ የገጠር ሴቶች አመራሮች እና ተወካዮች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ የዳያስፖራ ተወካዮች፣ የልማት አጋሮች እና የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ይሳተፋሉ። የቀኑ አከባበር አካል የሆነ የቴክኒክ ውይይት ትናንት የተካሄደ ሲሆን የአፍሪካ የገጠር ሴቶች መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ባለሙያዎች ሴቶችን ለማብቃት በየሀገራቱ እየተተገበሩ ያሉ ኢኒሼቲቮችን አስመልክቶ የእውቀት እና የተሞክሮ ልውውጥ አድርገዋል። ዛሬ በሚኖረው ዋናው የቀኑ አከባበር የከፍተኛ ባለስልጣናት ቁልፍ ንግግሮች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የገጠር ሴቶች ኢኒሼቲቭ የተሞክሮ ማጋራት መርሃ ግብሮች እና አውደ ርዕዮች ይካሄዳሉ። ሁነቶቹ የገጠር ሴቶች በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እና በግብርና መካናይዜሽን አማካኝነት የሚበቁባቸው የኢኖቬሽን አማራጮች የሚቀርቡባቸው ናቸው። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን ከአፍሪካ ህብረት የ2025 መሪ ሀሳብ ከሆነው “የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” የተሳሳረ መሆኑ ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የማሻሻሻ ፍትህ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል አካሄድ መሆኑን አመልክቷል። የቀኑን አከባበር ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የጋራ መግለጫው አፍሪካ ስርዓተ ጾታን ባማከለ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ስራ፣ የገጠር ሴቶችን በማብቃት እንዲሁም ማካካሻ ፍትህ እኩልነት የተረጋገጠበትና የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመገንባት ያላትን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያመላክት እንደሆነ ተገልጿል። የዓለም የገጠር ሴቶች ቀን የአፍሪካ ህብረት የስርዓተ ጾታ እኩልነት ለማረጋገጥ እና በማካካኛ ፍትህ አማካኝነት በገጠሪቷ የአፍሪካ አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። ህብረቱ ቀኑን ሲያከብር የበለጸገች፣ ሁሉን አቃፊ እና ዘላቂነትን ያረጋገጠች አህጉር ለመገንባት ባለው መሻት ውስጥ ሴቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ወደኋላ እንዳይቀሩ ዳግም ቃል ኪዳኑን የሚያድስበት እንደሆነ አመልክቷል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እ.አ.አ በ2007 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ባፀደቀው የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 62/136 አማካኝነት ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን እ.አ.አ ኦክቶበር 15 እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ በገጠር የሚገኙ ሴቶች ለግብርና፣ ምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ዘላቂ ልማት ያላቸው ወሳኝ አበርክቶዎች የሚዘከርበት ነው።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በሙሉ አቅም መተግበር ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው - መሐመድ አሊ ዩሱፍ
Oct 10, 2025 331
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ሙሉ ለሙሉ ገቢራዊ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 24ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሁነቶች በአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት እና ተወዳዳሪነት ተጽእኖ እያሳደሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከመቼው ጊዜ በላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሙሉ ለሙሉ በአፋጣኝ መተግበር እንደሚገባው የሚያመላክት ነው ብለዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ከቀረጥ ጋር ያልተያያዙ የንግድ ገደቦችን በማንሳት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተሳለጠ የንግድ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችሉ ማዕቀፎችን በመተግበር ለአጀንዳ 2063 መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኮሜሳ፣ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (ሳዴቅ) እና የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ (ኢኤሲ) የሶስትዮሽ ትብብር ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ማዕቀፉ የትስስር አጀንዳ ተምሳሌት እና አንድ የሆነች፣ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች አህጉር ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ የተስፋ ብርሃን ፈንጣቂ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር ቀጣናዊና አህጉራዊ የትስስር አጀንዳዎችን ትግበራ ለማፋጠን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንደሚያጠናክሩ ገለጹ
Oct 10, 2025 303
አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን የቆየ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። ጀርመን ለኢጋድ ቀጣና የተለያዩ የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፎችንም ይፋ አድርጋለች። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በልማት ትብብራቸው ዙሪያ በጅቡቲ ስትራቴጂካዊ ምክክር አድርገዋል። በምክክሩ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር እና ልማት ሚኒስቴር የምስራቅ አፍሪካ ዘርፍ ኃላፊ ሃኒንግ እና በጅቡቲ የጀርመን አምባሳደር ሄይከ ፉለር (ዶ/ር) ተገኝተዋል። ስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ የግንኙነት ማዕቀፎች ላይም መክረዋል። ፍልሰት እና አየር ንብረት ለውጥ የውይይቱ አበይት ማጠንጠኛዎች ናቸው። ሁለቱ ወገኖች የጀርመን ቀጣናዊ የፍልሰት ፈንድ ዳግም ማዋቀር ሂደት መልካም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በማንሳት የኢጋድ የቀጣናዊ የፍልሰት ፖሊሲ ማዕቀፍ ፣ የነጻ እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፎች እና የዜጎችን የአኗኗር ሁኔታ የማጠናከር ስራ ለመደገፍ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ጀርመን ለኢጋድ የፍልሰት ፖሊሲ ትግበራ ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ ትግበራ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ ቃል መግባቷን ኢዜአ ከቀጣናዊ ተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም ጀርመን በኢጋድ አባል ሀገራት ለሚከናወኑ የማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ስራዎች በቀጣናዊ የአደጋ ፋይናንስ ፕሮግራም አማካኝነት 22 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ መዘጋጀቷ ተመላክቷል። የፋይናንስ ማዕቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ድንገተኛ አደጋዎችን የመከላከል ስራዎች የሚደገፍ እና የኢጋድ የድርቅ አደጋን የመቋቋም እና ዘላቂነት ኢኒሼቲቭ ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን የሚደግፍ ነው። በስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች ውጤት ተኮር፣ አሳታፊ እና ተጠያቂነትን መሰረት ያደረገ አጋርነትን መፍጠር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢጋድ እና ጀርመን ትብብራቸውን ለማጠናከር፣ የጋራ ስራዎቻቸው የአባል ሀገራት የቅድሚያ ትኩረቶች ያማከሉ እንዲሆኑና የፖሊሲ ምክክራቸውን በመደበኛነት ለማከናወን ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ኢጋድ እና ጀርመን 37 ዓመታትን ያስቆጠረ አጋርነት እንዳላቸው መረጃዎች ያመለክታሉ።
የአፍሪካ ህብረት የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 7, 2025 372
አዲስ አበባ፤ መስከረም 27/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷ ወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን አስታወቀ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት ከፍተኛ አመራሮች ከሆኑት ዲያላ ሞሙኒ እና አህመድ ቤኒንግ ጋር በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል። የአፍሪካ ህብረት የወጣቶች ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ሊቀ መንበር ኡቺዚ ምካንዳዋየር በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል። የአፍሪካ ህብረት ስምምነቱ የአህጉሪቷ ወጣቶች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና ወጣቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። በስምምነቱ አማካኝነት የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት በሀገራት ደረጃ ያሉ የወጣት ምክር ቤቶች የሚያቀናጅ አህጉራዊ ማዕቀፍ እና ለአፍሪካ ወጣቶች እንደ ጋራ ድምጽ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ንቅናቄ የወለደው አህጉራዊ አደረጃጀት ሲሆን እ.አ.አ በ1962 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በጊኒ ኮናክሪ ባደረጉት ስብስባ ህብረቱን አቋቁመዋል። ህብረቱ የተመሰረተው በወቅቱ ወጣቶች አፍሪካ ከቅኝ ግዛት እንድትላቀቅ ለነበረው ትግል አቅም እንዲሆኑ ከማሰብ የመነጨ ነው። የወጣቶች ህብረቱ እንቅስቃሴ የፖለቲካ ድጋፍን በማሰባሰብ እና የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዲወጡ በማድረግ ረገድ ስትራጂካዊ ሚናውን ተጫውቷል። የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት እ.አ.አ በ2006 ባደረገው ስብስባ የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በድጋሚ የማደራጀት የውሳኔ ሀሳብ በማፅደቅ ህብረቱ የአህጉሪቷ የወጣት መዋቅር እንዲሆን በይኗል።
ሐተታዎች
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 74
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል። ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው። የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው። ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል። ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 350
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም። በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል። የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል። በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል። ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል። በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል። በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 543
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
"ያሆዴ"- ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት
Sep 28, 2025 635
(በማሙሽ ጋረደው - ከኢዜአ ሆሳዕና ቅርንጫፍ) የሀዲያ የአዲስ ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው። ለማህበራዊ የህይወት አመራር ጉልህ አስተዋጾም ስላለውም በሀዲያዎች ዘንድ በየዓመቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል፡፡ "ያሆዴ" ያለፈውን አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲስ ዘመን የሚቀበሉበት፤ የመጻኢ ተስፋ ብስራትና የልምላሜ ምልክትም ጭምር ተደርጎም ይቆጠራል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሲቀርብ የሀዲያ ተወላጆችና የበዓሉ ተሳታፊዎች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከያሉበት ወደአካባቢው በመምጣት ይሰባሰባሉ፡፡ በዘንድሮ የያሆዴ በዓልም የሀድያ ተወላጆች የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ በተዘጋጀ ስፍራ (ነፈራ) ተሰባስበው በዓሉን በድምቀት አክብረውታል፡፡ በበዓሉ አከባበር ያለፈው ዓመት ስኬትም ይገመገማል፤ በአዲሱ ዓመትም የተሻለ ተሰርቶ ስኬት እንዲመዘገብ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት ይካሄዳል። ሊተገበር የሚችል ዕቅድም ይታቀዳል፡፡ በግልና በቤተሰብ የመጡ ስኬቶች በጋራ በመሆን ይገመገማሉ። የበረቱና ውጤት ያስመዘገቡም እንዲበረታቱ ይደረጋል። ለዚህም ነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው የሚባለው። ሰዎች እንዲሰሩና ስኬት እንዲያስመዘግቡ የሚያበረታታ እሴት አለው። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፋን ቦጋለ እንደሚሉት የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል "ያሆዴ" ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት ነው፡፡ ከነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የበዓሉ መቃረብን የሚያበስሩት ታዳጊ ልጆች ናቸው። ልጆቹ የዋሽንት (ገምባቡያ) ድምጽ ማሰማት ከጀመሩ በጉጉት የሚጠበቀውን የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል መድረሱ ምልክት ነው። በዓሉ ሀድያዎች አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበት ወቅት ነው። በዓሉ የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት በመሆኑም የተለየ ትርጉምና ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች ተራርቀው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት ከያሉበት ይሰባሰባሉ። በዓሉ በአማረ መልኩ እንዲከበርም ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻቸውን ያከናውናሉ። አባውራዎች ለበዓሉ ሠንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በቱታ ወይም በቅርጫ ቡድናቸው አማካኝነት እየቆጠቡ ይቆያሉ። እንዲሁም ለእንስሳት የሚሆን የግጦሽ ሳር የሚያበቅል ቦታ ከልለው ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሚሆነበት ምክንያት ደግሞ በዓሉ በሚከበርበት ሰሞን የሰው ልጅ ይቅርና እንስሳትም መጥገብ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ እማውራዎች ከበዓሉ ሦስትና አራት ወራት አስቀድመው እንሰት በመፋቅ ቆጮና ቡላ ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም ከአካባቢው እናቶች በጋራ በመሆን (ዊጆ) የተሰኘ የቅቤ እቁብ በመግባት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ማጠራቀም ይጀምራሉ፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ ለአተካናና ለሥጋ መብያ ናቀሮ ወይም ዳጣን እንዲሁም የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት ድርሻ የእናቶች ነው፡፡ ለበዓሉ የቤት ውስጥና የውጭ ግርግዳን በቀለምና በተለያዩ ጌጣጌጦች የማስዋብ ሃላፊነት ደግሞ የልጃገረዶች ነው። ወጣት ወንዶች ከነሀሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚያሳዩዋቸውን ግንድ በመቁረጥ ለምግብ ማብስያ እንዲውል ፈልጠው ያዘጋጃሉ። በሀዲያዎች አጠራር ለችቦ የሚሆን እንጨት ወይም ጦምቦራ ከጫካ ለቅመው አስረው እንዲደርቅም ያስቀምጣሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት የሚያደርገው ጥረት በዓሉ በስኬትና በድምቀት እንዲከበር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በዚህም ያሆዴ ከተናጠል ይልቅ ትብብርን የሚያጠናክር ነው ማለት ይቻላል። እሴቱ በትብብር መድመቅ እንደሚቻልም የሚያሳይ ነው። ይህን ሀሳብ የሚጋሩት አቶ መስፍን የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል በምንም ሁኔታ መነጣጠል የማይቻል ትስስርን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ። ሀገራዊ አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር ዘመናትን የተሻገረና ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ባህላዊ እሴት ያለው መሆኑንም ይናገራሉ። በዓሉ ሊከበር ጥቂት ቀናት ሲቀረው አባውራዎች በቅርጫ ማህበራቸው አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ የእርድ በሬ ይገዛሉ። በዚህ ወቅት ገንዘብ ማዋጣት ያልቻሉ የቅርጫ አባላት እህል በሚደርስበት ወቅት ለመክፈል ተስማምተው በሬውን በዱቤ እንዲገዙ ይደረጋል፡፡ ይሄም የሚሆነው በያሆዴ በዓል አንዱ ሲበላ ሌላው ተመልካች መሆን ስለሌለበት ነው። እርስ በርስ መጨካከን እንዳይኖርና በዓሉን በአብሮነት ሁሉም ተደስቶ ማክበር እንዲችል ለማድረግ ነው። ከበዓሉ ዕለት በፊት ያለው የመጨረሻ ገበያም የእብድ ገበያ (መቻዕል ሜራ) የሚል ስያሜ አለው። ይሄ ሥያሜ ያገኘው በዓሉ ሲቃረብ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ውጥረት ታሳቢ በማድርግ ነው፡፡ በዚህ የእብድ ገበያ ህብረተሰቡ መገበያየት የሚጀምረው ጠዋት ማለዳ ጀምር ሲሆን የግብይት ሂደቱ የሚጠናቀቀው ደግሞ እኩለ ቀን ላይ ነው፡፡ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለመግዛትና የያሆዴ በዓል ከተከበረ በኋላ ለአንድ ወር ገበያ ስለማይቆም ይህን ታሳቢ ያደረገ ግብይት ለመፈጸም የግብይት ሂደቱ ጥድፊያ የበዛበት ሆኖ ይታያል። ያሆዴ በዓል መከበር የሚጀምረው በአተካን ሂሞ ወይም በአተካና ምሽት ሲሆን ይህም ከበዓሉ አንድ ቀን በፊት ያለው ምሽት ነው። ስያሜውን ያገኘው "አተካና" ከተሰኘና በያሆዴዎች ዘንድ ለክብር እንግዳ እና በዘመን መለወጫ ከሚዘጋጅ ምግብ ነው። አተካና ከወተት፣ ከአይብ፣ ከቡላ፣ ከቅቤና ከሌሎች የቅመማ ቅመም ውጤቶች የሚዘጋጅ ምግብ ሲሆን በጣም ጣፋጭና የምግበ ፍላጎትን የሚጨምር ምግብ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ይሄንን የተለየ ምግብ ተሰባስቦ በአብሮነት በመመገብ በደመቀ መልኩ በዓሉን ማክበር ይጀምራል፡፡ የአካባቢው አባቶች በወጣቶች የተዘጋጀ የማቀጣጠያ እንጨት (ሳቴ) ይዘው ትልቅ በሚባሉ አባውራ ቤት ደጃፍ ወደ ተዘጋጀው የችቦ ደመራ (ጦምቦራ) ቦታ ይመጣሉ:: የሀገር ሽማግሌች አዲሱ ዓመት የብርሃን ዓመት እንዲሆን፤ ለሀገርና ለህዝቦቿ ሰላም እንዲጸና፤ አብሮነት እንዲጠናከር፣ ሰላምና ፍቅር እንዲነግስ ፈጣሪያቸውን ከተማጸኑ በኋላ ችቦውን በእሳት ይለኩሳሉ፡፡ ችቦው ከተለኮሰ በኋላ የአካባቢው ወጣቶች ተሰባስበው ያሆዴ …ያሆዴ! …ያሆዴ! በማለት እየጨፈሩ ያነጋሉ ይጨፍራሉ:: በሀድያዎች ዘንድ "ያሆ" ማለት የአዲስ ዓመት መግባትን ተከትሎ ማብሰሪያ ጭፈራ ሲሆን "ኤዴ" ማለት ደግሞ አገናኝ ማለት ነው፡፡ በያሆዴ በዓል የእርድ ሥነ ስርዓት ለማከናወን ነዋሪዎች የሚሰበሰቡበት ስፍራ "ነፈራ" የሚል ስያሜ አለው። የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሰፋ ያለ ቦታ ሰሆን በተለያዩ የጥላ ዛፎች የተዋበና ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀም ነው። በእለቱ ለእርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኋላ የባህል ሽማግሌዎች የበሬውን ሻኛ በሰርዶ ሳር ለጋ ቅቤ ይቀባሉ፤ ወተትም ያፋሱበታል፡፡ ይህ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ጋቢማ የሚባል ሲሆን (የመልካም ምኞት) መግለጫ ስነ ስርዓትም ነው፡፡ ይህም ሥነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም "ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሀገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን " እያሉ በአባቶች ምርቃት ከተካሄደ በኋላ የእርድ ስነ ስርዓት ይከናወናል፡፡ የእርድ ሥነ ስርዓቱ የተከናወነበት ቤት እማወራ አስቀድመው ባደረጉት ዝግጅት መሰረት ቅቤ፤ (ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ) እንዲሁም ከታረደው የበሬ ሥጋ አርዚ ማራ (ቅምሻ) ይወሰድና ክትፎ ከተዘጋጀ በኋላ በጋራ እየበሉ እየተጫወቱ ይውላሉ፡፡ በዚህም በቅርጫ ሥጋው ላይ ከሚሳተፉት የቤተሰብ አባላት ውጪ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችም ጭምር አብረው በመብላት በመጠጣት በዓሉን በአንድነት ያሳልፋሉ፡፡ ቀሪውን የቅርጫ ሥጋም አባላቱ ተከፋፍለው ወደ እየቤታቸው ይወስዱታል፡፡ በዓሉ አብሮ የመብላት፣ የመጠጣት፣ የመጠያየቅ፣ ችግርንና ግጭትን በጋራ ተወያይቶ የመፍታት፣ መፈቃቀርና መተሳሰብን የሚፈጥር፣ አቅመ ደካሞችና የተቸገሩ የሚረዱበት የአብሮነት መገለጫ በመሆኑ በተለየ መልኩ ይከበራል፡ ከእርድ ሥርዓቱ በኋላ በማግስቱ ልጆች አደይ አበባ (ዘራሮ) ይዘው ወደ ወላጆቻቸው እየጨፈሩ ይመጣሉ። የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባላሉ። ከስጋውም፣ ከቦርዴውም፣ ከአተካናውም እንዲመገቡ ያደረጋል። ይህ ስነ ስርዓትም ሚክራ ይባላል። በያሆዴ የዘመን መለወጫ በዓል ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ሥጋና አደይ አበባ ጭምር ይዘው ይሄዳሉ። በዓሉ ያላገቡ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ለአዲስ ህይወት ጅማሬ የሚያበስሩበት በመሆኑን የተለየ ድባብ አለው፡፡ የያሆዴ በዓል ካሉት እሴቶች አንዱ የህብረተሰቡን የአካባቢ ልማት ተሳትፎ ማበረታታት ተጠቃሽ መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ዕሴቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናቅቀው ለማህበረሰብ ጥቅም እንዲውሉ ጭምር አቅም እየሆነ መምጣቱን ነው የሚናገሩት።ይህ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የማህበራዊ መስተጋብር መጋመጃ የሆነው በዓል እሴቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል መስራት ይገባል። እሳቸው እንዳሉት በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማስቻል እየተሰራ ነው፡፡ ለዚህም መምሪያው ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ዕሴቱን የመሰነድና ምርምሮች ማካሄድን ጨምሮ እያከናወናቸው ያሉ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 880
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1669
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2467
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2624
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 203
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 247
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6105
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4583
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ኢሬቻ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ማንሰራራት!
Oct 3, 2025 669
ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ሰዎች በክረምት ወቅት ከሚከሰት መለያየትና መራራቅ በኋላ ዳግም የሚገናኙበት፣ በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት ዕለት ነው። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። ኢሬቻ የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ጥብቅ ቁርኝት የሚገለጽበት የገዳ ስርዓት አንዱ አካል ነው፡፡ የኢሬቻ እሴቶች ጠንካራ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ያላት ሀገር ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው። አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ አብሮነት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ዕርቅ እና ሌሎችም ተጠቃሽ የመልካም እሴቶች መገለጫ ነው። በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አንዱ እሴት ኢሬቻ ሲሆን፤ ለሀገር ማንሠራራትና ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሠረት ይሆናል፡፡ ኢሬቻ አብሮነት የሚጸናበት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ይበልጥ የሚጎላበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጎለብትበት፣ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ማሰሪያ ከፍ ያለ በዓል ነው፡፡ ኢሬቻ በጋራ የሚያከብሩትና የዓለም ቱሪስቶች የሚታደሙበት ሲሆን፤ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል አከባበር ሀገራዊ ማንሰራራት በተግባር የተረጋገጠበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ዓለም የኢትዮጵያን መቻል በተግባር ባየበትና ሌሎች ለሀገር ማንሰራራት ዕውን መሆን መሠረት የሚጥሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኘሮጀክቶች ይፋ በተደረጉበት ማግስት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡ በዓሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመላው ኢትዮጵያዊያንን ሕብረት የሚንጸባረቅበት ሆኖ በተለያዩ አከባቢዎች በድምቀት እየተከበረም ይገኛል፡፡ በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Waaqa Uumaa, Waaqa Uumamaa ፍጥረትን የፈጠርክ ፈጣሪ Gurraacha garaa garbaa የእውነትና የሰላም አምላክ! Dogoggora nu oolchi ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! Dacheef nagaa kenni ለምድራችን ሰላም ስጥ! Laggeenif nagaa kenni ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! Olota keenyaaf nagaa kenni ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! . . . Loowan keenyaaf nagaa kenni " ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "አሜን! አሜን! አሜን!” ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 25 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ " ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት " በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" Irreecha Birraa (በውኃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን፤ በዓመቱ አጋማሽ ላይ "ኢሬቻ ቱሉ" Irreecha Arfaasaa ደግሞ በተራራማ ቦታ ይከበራል። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ነው። የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመምጣቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ይህ ከማህበራዊ መስተጋብር አኳያም ሰዎች የሚሰባሰቡበትና የሚገናኙበት ነው። ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ብርሃን (ብራ) ስለደረሰ ለዚያ ምልክት ይሆን ዘንድ የለመለመ እርጥብ ሣር ይዘው ወደ ወንዝ በመውረድ ንጹህ ውሃ ውስጥ እየነከሩና እየረጩ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ አብሮነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። ኢሬቻ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው "ዋቃ" "Waaqa" ምስጋናውን ለማድረስ የሚከበር ሲሆን፤ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲከበር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። ኢሬቻ የወንድማማችነትና የአንድነት አርማ ሲሆን፤ የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ፣ የህብረ ብሔራዊ አብሮነት ማስተሳሰሪያም ጭምር ነው፡፡ በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይበዛል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል፣ አንድነት ይጸናል። ኢሬቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ነው። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ስለሆነም ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር እንዲህ እያሉ ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። የበዓሉ ታዳሚዎች ከዋዜማው ጀምሮ በሆረ ፊንፊኔና በሆረ ሀርሰዲ በመሰባሰብ፤ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎችን በማዜምና ምስጋና በማቅረብ አድረው በነጋታው ዋናውን የምስጋና በዓልም ያከናውናሉ፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የደስታና የምስጋና ምልክት የሆነውን ባህላዊ ነጫጭ ልብስ ለብሰው፣ ባህልን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ሁነቶችን በመከወን ልዩ ልዩ ዜማዎችን በማዜም፣ ግጥሞችን በማቅረብ፣ ወደ ፈጣሪ በመጸለይ እና ምስጋና በማቅረብ ሥርዓቱን ያከናውናሉ፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ከማቀራረብና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጾኦ ያለው ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገር የመጡ ልዑካን በበዓሉ ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። የኢሬቻ በዓል ለቱሪዝም ፍሰት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ጉልህ ነው፤ በርካታ የባህር ማዶ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የሚታደሙበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ ሲሆን፤ ዘርፉን በማጠናከር እና ብሔራዊ ልማትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚናንም የሚጫወት ነው፡፡ ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!
በትግራይ ክልል የመስቀል በዓል አከባበር
Sep 27, 2025 733
የመስቀል በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በልዩ ድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ ነው። በዓሉ እንደየአካባቢው ባህላዊና ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል። በትግራይ ክልልም የመስቀል በዓል እንደሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሁሉ በናፍቆት ከሚጠበቁና በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት ተርታ ይመደባል። ለዚህም ሲባል የተለያዩ ዝግጅቶች ከበዓሉ ዋዜማ በፊት እንዲጠናቀቁ የሚደረግ ሲሆን፥ በተለይ በየዓመቱ መስከረም 16 እና 17 ዘመድ አዝማድ ተጠራርተው የሚገናኙበት የፍቅርና የአብሮነት በዓል ሆኖ ይከበራል። የክርስቶስ ግማደ መስቀል በንግስት ኢሌኒ አማካኝነት መገኘቱን በማሰብ በየዓመቱ መስከረም አጋማሽ ላይ የሚከበረው የመስቀል በዓል የመስቀል ኃያልነት፣ እውነት በተደበቀበት ለዘላለም እንደማይቀርና ፍቅርን አብዝቶ የሚሰበክበት ከዚህ ባለፈም እርቅ የሚወርድበትና ደስታ የሚገለጽበት አጋጣሚ መሆኑም ይገለጻል። በትግራይ የበዓሉን ታላቅነትና ክብር ለማድመቅ ምእመናን ጽዱ ልብስ ለብሰውና የተለያዩ ዝማሬዎችን በማሰማት ደመራ ወደሚደመርበት ሥፍራ ችቦ ይዘው በመሄድ ደምራውን በማቀጣጠል የሚያከበሩት ሲሆን፣ በእለቱ የቤት እንስሳት ጭምር ቀንዳቸውና ጀርባቸው ላይ ቅቤ ተቀብተው እንዲያርፉ ይደረጋል። ዘመድ አዝማድ፣ ጎረቤታሞች፣ አብሮ አደጎችና የበዓሉ ታዳሚ እንግዶችም ተሰባስበው ማለዳ ላይ ገንፎ በማዘጋጀት ይመገባሉ። የእንስሳት እርድ በማከናወን ባህላዊ መጠጦችን በማዘጋጀት በዓሉን የፍቅር፣ የመሰባሰብ፣ የአንድነትና ተካፍሎ የመብላት በዓል መሆኑን በተግባር የሚያሳይበት ክስተት ሆኖ ያልፋል። "ዓኾይ ዓኾኾይ" የጎመን ምንቸት ውጣ የገንፎ ምንቸት ግባ በማለትም ችቦ ተሎኮሶ በየቤቱ በመዞር የምረቃ እና ለሚቀጥለው ዓመትም በሰላምና ደስታ እንዲሁም እድሜና ጤናን በመመኘት ይከወናል። የአደባባይ በዓል የሆነው የመስቀል በዓል በዝማሬ፣ በሆታና እልልታ የሚገለጽ ሲሆን፤ ወርሃ መስከረም እሸት አሽቶ አበቦች አብበውና ምድር ልዩ ልምላሜን ተላብሶ የሚታይ በመሆኑ ልክ በታሪኩ እንደሰፈረው የሰላም፣ የእውነትና የአንድነት በዓል መሆኑን በተግባር የሚታይበት ነው።