ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ትህነግ ሕዝብን በርሃብ በመቅጣት ለፖለቲካ መሳሪያነት የመጠቀም ተግባሩን ዳግም በትግራይ ህዝብ ላይ እያሳየ ነው
Dec 25, 2025 23
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 16/2018(ኢዜአ)፦ ትህነግ ሕዝብን በርሃብ በመቅጣት ለፖለቲካ መሳሪያነት የመጠቀም ተግባሩን ዳግም በትግራይ ሕዝብ ላይ እያሳየ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽነር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) ተናገሩ። የትህነግ ቡድን የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል በመጠለያ ማዕከላትና በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር የሚያቀርበውን ሰብዓዊ ድጋፍ ለተፈለገው ዓላማ እንዳይውል እያደረገ እንደሚገኝም የሰሞኑ የህፃፅ መጠለያ ጣቢያ ማስረጃ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የትህነግ ህገወጥ ቡድን የትግራይን ሕዝብ መሠረታዊ ፍላጎቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች ለፖለቲካ ዓላማ የመጠቀም ልማድ አዲስ ክስተት ሳይሆን የቀደመ ታሪኩና መገለጫው ነው። ትህነግ የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ለመሳብ በትግራይ ክልል በመጠለያ ጣቢያዎች ለሚገኙ ወገኖች የሚቀርብን ሰብዓዊ ድጋፍ በመንጠቅ ድራማዊ ፕሮፓጋንዳ እያስተጋባ መሆኑንም አስረድተዋል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም የፌደራል መንግስት በግልጽ መረጃና ማስረጃ የሚልከው ሰብዓዊ ድጋፍ የት እንደገባ መጠየቅ እንዳለበት እና በቡድኑ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ መደናገር እንደሌለበትም አንስተዋል። ትህነግ ሰብዓዊ ድጋፍ ለፖለቲካ ዓላማ ለማዋል የሚያደርገውን ጥረት ሁሉም ሊገነዘበው እንደሚገባም ጠቅሰዋል። የፌደራል መንግስትም በትግራይ ክልል አስተማማኝና ቀጣይነት ያለው ሰብዓዊ ድጋፍ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በዚህም በትግራይ ክልል ከባለፈው ጥር 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታኅሳስ ወር 2018 ዓ.ም ድረስ ሁለት ሚሊየን ኩንታል በገንዘብ ሲተምን 32 ቢሊዮን ብር የሚገመት ሰብዓዊ ድጋፍ መሰራጨቱን አስታውቀዋል። ይህም የፌደራል መንግስት ዜጎች ሰብዓዊ ጉዳት እንዳይደርስባቸው ያለውን ጠንካራ አቋም በተግባር የሚያረጋግጥ መሆኑንም ነው ያብራሩት። የትህነግ ቡድን በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፉ ተደራሽ እንዳይሆን በማስተጓጎል፤ ድጋፉን ከችግረኛ ዜጎች በመንጠቅ ዳግም የሕዝብ ጠላትነቱን እያረጋገጠ እንደሚገኝም አብራርተዋል። ቡድኑ ይህ አልበቃ ብሎት ለእያንዳንዱ ድጋፍ ፈላጊ ዜጋ ከሚሰጥ የፍጆታ ድርሻ ላይ መዋጮ እንደሚሰበስብም ነው የተናገሩት። ትህነግ በሰብዓዊ ድጋፍ ስም በዜጎች ላይ የሚፈጽመው አስነዋሪ ድርጊት ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ያለውን የተላላኪነት ጥግ በተግባር ያረጋገጠ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ኮሚሽኑ የድጋፍ ጥሪ ባላቀረበበት ሁኔታ በማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች በቡድንም ሆነ በተናጠል የሚደረጉ የድጋፍ ማሰባሰብ ዘመቻ የአሰራር ስርዓትን የጣሱ ህገ-ወጥ አካሄዶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በዚህም የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም ሰብዓዊ ድጋፍ በማሰባሰብ ላልተገባ ዓላማ እያዋሉ የሚገኙ አካላት ከድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በእንስሳት ሃብት ልማት የአርሶ አደሮችን ምርታማነትና ዘላቂ ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Dec 25, 2025 33
ባቱ፤ ታህሳስ 16/2018(ኢዜአ)፦ በእንስሳት ሃብት ልማት የአርሶ አደሮችን ምርታማነትና ዘላቂ ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። ምርታማነታቸውና ውጤታማነታቸው የተረጋገጠ የተሻሻሉ የላም ዝርያዎች በምስራቅ ሸዋ ዞን ለሚገኙ አርሶ አደሮች ተላልፈዋል። በመርሃ ግብሩ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሣ(ዶ/ር)፤ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን ለአርሶ አደሮች ተደራሽ በማድረግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዘንድሮው ዓመት ብቻ 5 ሚሊየን የወተት ላሞችን ለማዳቀል ታቅዶ እስካሁን 2 ሚሊየን ማዳቀል መቻሉን ጠቅሰው በዘርፉ ልማት በትኩረት በመስራት የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ከማሳደግ አንፃር በዶሮና የዓሣ ልማት እንዲሁም የንብ ማነብ ዘርፎች ላይ ተመሳሳይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በኦሮሚያ ክልል የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በዝሪያ ማሻሻያ ላይ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ ጌቱ ገመቹ ናቸው። ባለፈው ዓመት በክልሉ 2 ነጥብ 6 ሚሊየን ላሞችን በማዳቀል ከ400 ሺህ በላይ ዝርያቸው የተሻሻሉ ጥጆች መወለዳቸውን አንስተዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም ላሞችን በሰው ሰራሽና በመደበኛ የማዳቀል ስራ በብዛት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም የዘርፉን ልማትና ተጠቃሚነት የማሳደግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው የዛሬው መርሃ ግብርም የዚሁ ጥረት አካል ነው ብለዋል። የምስራቅ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አባቡ ዋቆ፤ በዞኑ በተለይም የሌማት ትሩፋትን በማስፋፋትና ሌሎች የልማት ስራዎችን አቀናጅቶ በመስራት ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮው ዓመት በዞኑ ከ59ሺህ በላይ ሰዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን አንስተው የእስካሁኑ ሂደት ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ ከእንስሳት ሃብት ልማት በተጨማሪ በበጋ መስኖ ስንዴ፤ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በሌሎች የሰብል አይነቶች ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት እንዲችሉ ትኩረት ተደርጓል
Dec 25, 2025 33
ጎንደር፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ) ፡-በአማራ ክልል የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት እንዲችሉ ትኩረት መደረጉን የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና በጎንደር ከተማ ዛሬ አስጀምሯል፡፡ የቢሮው ኃላፊ ስብሁ ገበያው (ዶ/ር) በስልጠና ማስጀመሪያው ላይ እንደገለጹት አዲሱ የስልጠና ፖሊሲና ስትራቲጂ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ገበያው የሚፈልገውን የሰው ኃይል በማምረት ላይ እንዲያተኩሩ የሚያስችል ነው። ስልጠናው ፖሊሲና ስትራቴጂው በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ ተመስርቶ ሀገር በቀል እውቀትን ማጎልበት ላይ እንዲያተኩር በማድረግ ወጣቱን ትውልድ መጥቀም ዓላማው ያደረገ ነው ብለዋል። የአለም ሀገራት እድገትና ብልጽግናቸውን ማረጋገጥ የቻሉት በመካከለኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሃይል ማፍራት ላይ በመስራታቸው ነው ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው፡፡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ኢኮኖሚውን የሚደግፉና ሀገር ገንቢ ትውልድ የሚያፈሩ በመሆናቸው የከተማ አስተዳደሩ ድጋፍና ትብብር በማድረግ ተቋማቱን የማጠናከር ስራ እንደሚሰራም አመልክተዋል። የጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተስፋሁን መኮንን በበኩላቸው አዲሱ ፖሊሲና ስትራቴጂ ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ለትምህርትና ስልጠና ጥራት መረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ለተግባር ልምምድ ልዩ ትኩረት የሰጠና አለም አቀፍ ሁኔታዎችን ባገናዘበ መንገድ በገበያ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል። ኮሌጁ በየዓመቱ ከሶስት ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ገበያ ተኮር በሆኑ የሙያ መስኮች አሰልጥኖ በማብቃት አምራች ኢንዱስትሪውን እየደገፈ እንደሚገኝም ገልጸዋል። ለአራት ቀናት በሚቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ላይም የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ከጎንደር ከተማ፣ ከማእከላዊና ከሰሜን ጎንደር ዞኖች የተውጣጡ የመንግስትና የግል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ዲኖች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
አስተዳደሩ ዲጂታል ማንነትን መሰረት ያደረገ ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የተሟላ ሥርዓት እየዘረጋ ነው
Dec 25, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 16/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲጂታል ማንነትን መሰረት ያደረገ ዘመናዊ አገልግሎት አሰጣጥን ማሳለጥ የሚያስችል የተሟላ ሥርዓት እየዘረጋ መሆኑን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትግበራን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት፤ ዲጂታል 2030 ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን መገንባት ቁልፍ የስትራቴጂው ግቦች እንደሆኑ አስረድተዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ አስተዳደሩ የሚሰጣቸው የመንግስት አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግ ሰፋፊ ስራዎችን በማከናወን ላይ ነው። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በፈጠረው መደላድልም ተቋማትን የማገናኝትና እንዲናበቡ የማድረግ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በተጨማሪም በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል በማዘጋጀትም የተገልጋዩን የአገልግሎት እርካታ ማሳደግ የሚያስችል አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀቱን አብራርተዋል። በመሆኑም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በመዲናዋ በሁሉም ተቋማት ዲጂታል ማንነትን ማሰረት ያደረጉ አገልግሎቶች የሚሰጡበት የተሟላ ስርዓት እየተዘረጋ መሆኑን ነው የገለጹት። ከተማ አስተዳደሩ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አኳያ ራሱን በመቃኘት የነዋሪዎችን የዲጂታል መታወቂያ መረጃን የማዋሀድ ስራ እንደሚሰራም ነው የጠቀሱት። በመዲናዋ የተለያዩ ተቋማት በሚሰጡ የኤሌክትሮኒክ አገልግሎቶች ነዋሪው ባለበት ሆኖ የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ በማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው የገለጹት። በዋናነትም የሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎትም ከፋይዳ መታወቂያ ጋር እንዲያያዝ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት መደላድል መፈጠሩን አብራርተዋል። የስማርት ሲቲ መገለጫ ዲጂታል አገልግሎትን በተሟላ መልኩ መስጠት ነው ያሉት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ የነዋሪነትና የሲቪል ምዝገባ ስርዓቱ ፍትሐዊ፣ ተጠያቂነት ያለበት፣ ተደራሽና ዘመናዊ ለማድረግም እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በዘንድሮው በጀት ዓመት ማጠናቀቂያ በአጠቃላይ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ሙሉ ለሙሉ የፋይዳ መታወቂያ እንዲይዙ ይደረጋል ነው ያሉት። የሚሰጡ አገልግሎቶች ዲጂታል እንዲሆኑ መደረጉ ብልሹ አሰራርን ለማስቀረትና ፈጣን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑንም አንስተዋል።
በክልሉ የመማር ማስተማር ስራ ቅድሚያ የሚሰጠው ቁልፍ የልማት ተግባር ሆኖ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Dec 25, 2025 42
ባህር ዳር፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥና ተደራሽነትን ማስፋት ቅድሚያ የሚሰጠው ቁልፍ የልማት ተግባር ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ አረጋ ከበደ ለምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ እንዳሉት፤ የትምህርት ዘርፉ ከልማቶች ሁሉ ቅድሚያ የሚሰጠው የዘላቂ እድገት አቅም ነው። በመሆኑም በክልሉ የመማር ማስተማር ስራው ቅድሚያ የሚሰጠው ቁልፍ የልማት ተግባር ሆኖ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ የተስተዋለው የሰላም መታጣት ችግር በመማር መስተማር ስራው ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩን ጠቅሰው፤ ችግሩን በመቋቋም የተሰራው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ገልፀዋል። አሁንም የመማር ማስተማር ስራውንም ሆነ ሌሎች የልማት ስራዎችን የበለጠ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሰላምን በዘላቂነት የማስፈኑ ስራ በተጀመረው አግባብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ለመማር ማስተማር የሚያግዙ ግብዓቶችን በማሟላት፣ ከደረጃ በታች የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል፣ በቴክኖሎጂ የታገዙ አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን በመገንባትና መሰል ለትምህርት ጥራት እንዲሁም ተደራሽነት የሚያግዙ ተግባራት ከየትኛውም ልማት ቅድሚያ ተሰጥቷቸው ይከናወናሉ ብለዋል። የትምህርት ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ሁሉ እገዛና ትብብር በማድረግ የትምህርት ተቋማትን በባለቤትነት በመገንባትና ግብዓት በማሟላት የሚጠበቅበትን ሚና ሁሉ ሊወጣ እንደሚገባም አሳስበዋል። የትምህርት ቤት ምገባ ለትምህርት ሽፋን ማደግና ጥራት መረጋገጥ እያገዘ መሆኑን ጠቅሰው፤ አሁንም የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ ከመንግስት ባለፈ ባለሃብቱና ማህበረሰቡ በንቅናቄ ሊሰራው ይገባል ብለዋል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ በበኩላቸው፤ ለመማር መስተማር ስራው የሚያግዙ ግብዓቶችን በተቻለ አቅም ለማሟላት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። ተደራሽነትን ለማረጋገጥም የ63 ትምህርት ቤቶች ግንባታ መጀመሩን ጠቅሰው፤ ማህበረሰቡን በማስተባበር በራሱ አቅም ትምህርት ቤቶችን ገንብቶ ለአገልግሎት እንዲያበቃ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል። በአሰራር የሚስተዋሉ ክፍተቶችንና የግብዓት አለመሟላትን በጥናት ላይ መሰረት ያደረገ ምላሽ ለመስጠትም ቡድን ተዋቅሮ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። ምክር ቤቱ የክልሉን የ5 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ከገመገመ በኋላ ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጡም ተመልክቷል።
ፖለቲካ
የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ነው
Dec 25, 2025 88
ባሕርዳር ፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ) ፡- የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር፤ አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔ በባሕርዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፤ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በቅርቡ የተፈራረመው የዘላቂ ሰላም ስምምነት በክልሉ ሰላምን ለማፅናት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የክልሉ መንግስት ችግሮችን በውይይትና በንግግር መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲያቀርብ የነበረው የሰላም አማራጭ ፍሬ ማፍራቱን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል። ግጭት ይብቃ ብለው የክልሉን መንግስት የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለተመሰሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን ምክር ቤቱ ያመሰግናል ያሉት አፈ ጉባኤዋ ፤ ሌሎች በጫካ የቀሩ ታጣቂዎችም የሰላም ጥሪውን ተቀብለው እንዲመጡ ጠይቀዋል። የአማራ ክልል መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን ገልጸው ፤ አጠናክሮ እንዲቀጥል በምክር ቤቱ በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ትብብር የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክር ቤት አባላት ለመልካም አስተዳደር መስፈን፣ ለዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበርና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተያዘው ዓመት የሚካሄደው 7ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተአማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅና ህዝቡ በምርጫው በንቃት እንዲሳተፍ የምክር ቤት አባላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። ምክር ቤቱ የክልሉን ትምህርት ቢሮ የ5 ወራት እቅድ አፈፃፀምና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በተከናወኑ የፋይናንስ ህጋዊነትና ክዋኔ ኦዲት ግኝቶች ላይ እንደሚመክር ከመርሃ ግብሩ መረዳት ተችሏል። በጉባዔው ልዩ ልዩ አዋጆችና ሹመቶች እንደሚጸድቁም ይጠበቃል።
የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ ለውጦችን በሚያሳይ መልኩ ይከበራል
Dec 25, 2025 98
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ ከጥር 15 እስከ 19 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከበር በኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ ገለፁ። በበዓሉ ላይ "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በሚል የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብም ተመላክቷል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ፤ የአየር ኃይሉን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል መሪ ሃሳብ ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ደማቅ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር አስታውቀዋል። በበዓሉ ከጥር 15 ቀን ጀምሮ በሚካሄደውና "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በተሰኘው መርሃ ግብር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብ አመላክተዋል። በዚህም የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ የሩሲያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይሎች በጋራ በመሆን የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት እንደሚያቀርቡ ጠቅሰዋል። "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ የቻይና፣ ህንድ፣ አሜሪካ እና ደቡብ አፍሪካ ግዙፍ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ኤክስፖ እንደሚካሄድም ገልፀዋል። ከ25 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ የቴክኖሎጂ ተቋማት የደረሱበትን ደረጃ ለጉብኝት ክፍት የሚያደርጉበት "ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2026" እንደሚካሄድም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የአቪዬሽን ማዕከል መሆኗን የምታረጋግጥበት "ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም" ለሶስተኛ ጊዜ እንደሚካሄድም ተናግረዋል። "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው መድረክ ላይ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦችና ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች ይታደማሉ ነው ያሉት። የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አዛዦችና የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል ርዕስ ከህዝቡ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ጠቅሰዋል። በዓሉ የአየር ኃይሉን የ90 ዓመት የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በማሳየት ይከበራል ነው ያሉት። መላው የሀገሪቱ ህዝብ በዚህ ታሪካዊ በዓል ላይ በመገኘት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የደረሰበትን ዝግጁነት እንዲመለከት ጥሪ አቅርበዋል። የበዓሉ አካል የሆነና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ሃሳብ ባሳለፍነው ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ የ10 ኪሎ ሜትር ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ሩጫ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይህ ውድድር በህዝብና በተቋሙ መካከል ያለውን ትስስር ያጠናከረና ለዋናው በዓል መሰረት የጣለ ታሪካዊ ኹነት ሆኖ ማለፉንም ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
Dec 25, 2025 64
ባሕር ዳር፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔውን መካሄድ ጀምሯል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ የአምስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለጉባዔው ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል። በውይይቱ በትምህርት አጀማመርና በተከናወኑ ተግባራት ላይ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ተጠቁሟል። እንዲሁም በክልሉ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የፋይናንስ ሕጋዊነትና የክዋኔ ኦዲት ግኝቶችንና የተሰጡ የማሻሻያ ሐሳቦችን የሚያሳይ የተጠቃለለ ሪፖርት ላይ እንደሚመክር ተመላክቷል። ጉባዔው ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፤ በቆይታው ልዩ ልዩ ዐዋጆች እና ሹመቶችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።
መንግሥት ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል-የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Dec 24, 2025 159
አዲስ አበባ፣ታኅሣስ 15/2018(ኢዜአ)፡-መንግሥት የሀገር ግንባታ ሂደቱን ለማጽናት እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል፡፡ እነዚህ ሦስቱ ምሰሶዎች ሀገራዊ አንድነትን፣ሰላምና ብልጽግናን፣ እንዲሁም ዜጎች በመተማመን እና በተጠያቂነት ላይ የተመሠረተ የጋራ ራዕይ እንዲኖራቸዉ የሚያደርጉ ቁልፍ መሰረቶች ናቸው፡፡ ዲሞክራሲን የመገንባት ሂደት ለአንድ ሀገር ወሳኝ ተግባር ሲሆን፣ በዋናነት ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቁ ተቋማትን ማቋቋም ላይ ትኩረት ያደረገ ነዉ፡፡ተቋማቱ የሚመሩባቸዉ ህጎችና የአሰራር ሥርዓቶች፣የተቋማቱ አወቃቀርና አደረጃጀት፣ እንዲሁም ለህዝብ ያላቸዉን ተዓማኒነትን መጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራበት ይገኛል፡፡ ጠንካራ የዲሞክራሲ ባህልና ሥርዓት የሚገነባው ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት ሲፈጠሩና ሲጠናከሩ መሆኑን መንግሥት በጽኑ የሚገነዘበው ጉዳይ ነዉ፡፡በዚህም ኢትዮጵያ ባለፉት 7 ዓመታት በዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ሂደት ውስጥ ሁለተናዊ ሪፎርም ሥራዎችን ስታከናውን ቆይታለች፡፡ እነዚህ ሪፎርሞች የሀገሪቱን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑትን የዲሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እና ጠንካራ አድርጎ ለመገንባት መንግሥት ምን ያህል ቁርጠኛ እንደሆነ ያሳየባቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ተቋማት መጠናከር በአንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም እና ልማት እንዲረጋገጥ እንደ ዋንኛ ምሰሶ የሚወሰድ ነው፡፡ በተለይም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ የታዩ ተጨባጭ ለውጦች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ለመጠበቅ፣ እንዲሁም የሕዝቡን ዕምነት ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ መንግሥት በተለይ ተቋማዊ ዐቅምን በማሳደግ እና ነፃነትን በማረጋገጥ፣ የዲሞክራሲ ምህዳርን እንዲሰፋ ለማደረግ የሚጠበቅበት ግዴታ ብቻ ሳይሆን ዲሞክራሲ የሚያብብበትን አስቻይ ዐውድና ማዕቀፍ ለመፍጠር ዓለማው አድረጓል፡፡ ይሄንን ከግብ ለማድረስ በተለይ የፀጥታ፣ የፍትሕ፣ የሲቪልና የሚዲያ ተቋማት፣ እንዲሁም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕዝብን ማዕከል አድርገው እንዲሰሩ መንግሥት በቁርጠኝነት በመደገፉ እንደ ሀገር ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ በማደርረግ ተጨባጭ ዉጤቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል፡፡ ሌላው መንግስት በትኩረት እየሰራበት ያለው ጉዳይ እንደ ሀገር ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ነዉ፡፡ ይህ ሂደት ዋና ዓለማ ያደረገው መላዉ ሕዝብ፣ ተቋማት፣ አመራርና ሠራተኛዉ በሀገራዊ ራዕይ ላይ በተለያዩ ድምጾች የጋራ እድገትን በመገንባት ሀገራዊ ህለውና እና ብልጽግና እንዲረጋገጥ እንዲሁም በዜጎች መካከል መተማመን እና ሀገራዊ አንድነትን እንዲፈጠር ማድርግ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ የብዙሃን ድምጽ የሚሰማበት የፖለቲካ ዐዉድ ለመፍጠር አያሌ የፖለቲካ ማሻሻያዎችን አድርጋለች፡፡ በዚህም እስከዛሬ በነበሩ መንግሥታት ያለተሞከረውን ጫፍ ወጥተው የሚታዩ ተቃርኖ ሀሳቦችን ለማጥበብና ለማቀራረብ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም፣ ሀገራዊ የውይይት መድረክ እንዲፈጠር ተደርጓል፡፡ በዚህም ገና ከወዲሁ በርካታ ለዉጦች እየታዩ ሲሆን ውሳኔው ለምንመኛት የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን የማዕዘን ድንጋይ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ በአጠቃላይ መንግሥት መልአተ ሕዝቡን በማስተባበር ጠንካራና ብልጽግናዋን በልጆቿ ያረጋገጠች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እያደረገ ባለው ዘርፈ ብዙ ጥረት ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን የመፍጠርን ጉዳይ በልዩ ትኩረት የሚሰራበት ዋንኛው አጀንዳው ሆኖ ይቀጠላል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ
Dec 24, 2025 198
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 15/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ ገጽ ይፋ ሆኗል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን የዝግጅትን በ etaf90years.com ድረ-ገፅ አማካኝነት አጠቃላይ መረጃ ማግኘት እንደሚቻል ተቋሙ አስታውቋል። የምስረታ ቀን በዓሉ ላይ ኅብረተሰቡ እንዲሳተፍም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባወጣው መግለጫ ገልጿል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓሉን አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል:- ነሐሴ 12 ቀን 1921 ዓ.ም የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ የገባ ቢሆንም አየር ኃይላችን እንደ ተቋም አደረጃጀት ይዞ በይፋ የተመሰረተው ሕዳር 20 ቀን 1928 ዓ.ም ኢትዮጵያዊው ሻለቃ ሚሽካ ባብቼፍ የአየር ኃይል አዛዥ ሆነው በተመደቡበት ቀን ነው፡፡ ጀግናው የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90 ዓመታትን ባስቆጠረው የምስረታ ታሪኩ በየዘመናቱ ሁሉ የሀገርን ሉዓላዊነት በመጠበቅ አኩሪ ታሪክ ያለው ስመ ገናና ተቋም ነው፡፡አየር ኃይላችን የኢትዮጵያን የአየር ክልል በጀግንነት ከመጠበቅ ባሻገር በዓለም አቀፍ የሠላም ማስከበር ተልዕኮዎች በመሰማራት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ አውለብልቧል፡፡ የሠላም አምባሳደርነቱንም በተግባር አሳይቷል፡፡ በድል እና በመስዋዕትነት የደመቀ ታሪክም አኑሯል፡፡ በስልጠናው ዘርፍም ከራሱ አልፎ የሌሎች ሀገራት የአየር ኃይል ሙያተኞችን ማሰልጠኑን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ 90ኛ ዓመት የአየር ኃይል የምስረታ ቀን በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል ዋና መሪ ቃል ከጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድርስ በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድምቀት ይከበራል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር የጀመረ ሲሆን የዚሁ አካል የሆነውና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ቃል ሕዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ዓለም አቀፍ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በድምቀት ተካሂዷል፡፡ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ታላቅ አየር ኃይል እየተገነባ ነው -ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ይህ የሩጫ ውድድር ህብረተሰቡ በከፍተኛ መነቃቃት የተሳተፈበት፣ ተቋሙና ህዝቡ የተሳሰረበት፣የቱሪስት መዳረሻ የሆነችው ቢሾፍቱ ከተማ የተዋወቀችበት ከመሆኑም ባሻገር በቀጣይ ለሚካሄዱት ኩነቶች የአየር ኃይል የምስረታ ቀን ዋናው በዓል መሰረት ጥሎ ያለፈ ታሪካዊ ውድድር ነው፡፡ በመቀጠል ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ዓ.ም ጀምሮ የሚኖረው የሚከተሉትን ኩነቶች የያዘ ነው የመጀመሪያው በዓይነቱ ለየት ያለ እና ለሁለተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አየር ኃይል አዘጋጅነት ‘የአንበሶች ሠማይ! ኢትዮጵያ’ በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአየር ኃይል፣ የሩሽያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ የአየር ኃይል እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይል በጋራ የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት 2026 በድምቀት የሚካሄድ ይሆናል፡፡ በመቀጠል በከፍተኛ ጉጉት የሚጠበቀው "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የቻይና፣ የህንድ የአሜሪካ እና የደቡብ አፍሪካ ታላላቅ ኩባንያዎች ብሎም ከ 25 በላይ የሚሆኑ በአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት የአቪዬሽንና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ2026 ይካሄዳል፡፡ የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓል ከሚያከናውናቸው ኩነቶች አንዱ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦች የሚሳተፉበት እና "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ለ3ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አየር ኃይል አዘጋጅነት ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች በተገኙበት የሚካሄድ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ ከአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ጋር ያላትን ቅርብ ትስስር በተግባር የሚያረጋግጥ ይሆናል፡፡ አየር ኃይል የሀገርን ሉዓላዊነት በማስከበር አኩሪ ታሪክ አለው- ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓል ከሚካሄዱ መርሃ ግብሮች መካከል የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ የጦር አዛዦች እንዲሁም የሀገራችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል መሪ ቃል ከህብረተሰቡ ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ሕዝባዊ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ የበዓሉን የአከባበርን ሁኔታ የሚገልፅ እና የአየር ኃይልን ታሪክ የበለጠ የሚያሳውቅ፣ የዝግጅቱን ዝርዝር የሚያሳይ እንዲሁም የባለፉት ዓመታትን የተቋሙን የለውጥ ሂደት የሚያስቃኝና etaf90years.com የተሰኘ የኢቨንት ድረ ገፅ ያለው ሲሆን በዚሁ ድህረ ገፅ ሁሉንም የበዓሉ ኩነቶች ማግኘት የመግቢያ ቲኬት መግዛትና በድረ ገፅ ኩነቶቹን መከታተል ይቻላል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል በ90 ዓመት ጉዞው ለኢትዮጵያችን መስዋዕትነት ከፍሏል፡፡ የኢትዮጵያን የአየር ክልል በጀግንነት ጠብቋል፡፡ ሀገር አፅንቷል፤ ሀገር አሻግሯል፡፡ በእሳት ተፈትነው ያለፉ ብዙ ጀግኖችንም አፍርቷል፡፡ በውጊያ መሰረተ ልማት፣በሰው ኃይል ግንባታና ትጥቅ በማሟላት ኢትዮጵያን የሚመጥን ተቋም እየተገነባ ነው የከበረ እና የገዘፈ ታሪክ ያለው የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓሉን ሲያከብርም ያለፈውን ለመዘከር አሁናዊ የተቋሙን ቁመና ለማቀብ፣ የደረሰበትን ሁሉን አቀፍ ዝግጁነት ለማሳየት፣ የሀገራችንን ገጽታ በማጉላት እና የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ተስፋ ለማነሳሳት በሚያስችሉ ዝግጅቶች እንዲሁም ተግባራት የሚከበር መሆኑ ተመላክቷል። ኅብረተሰቡ በዓሉ ላይ እንዲገኝና በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባል ሆነው ያገለገሉትንና እያገለገሉ ያሉ ጀግኖችን እንዲያከብር፣ እንዲዘክር፣ የሀገር መመኪያና ኩራት የሆነው ተቋም እንዲመለከትና በዚህ አስደናቂና ታሪካዊ በዓል ላይ እንዲታደም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጥሪውን አቅርቧል፡፡
ልማት ላይ በመሳተፍ የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል - የቀድሞ ታጣቂዎች
Dec 24, 2025 169
መተማ፤ ታህሳስ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በሰላም ግንባታና ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል ሲሉ በምዕራብ ጎንደር ዞን የሰላም አማራጭን ተቀብለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች ገለጹ። በዞኑ መተማ ወረዳ ጉባይና ሌንጫ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ታጣቂዎቹ የሰላምን አማራጭ ተቀብለው ሲመለሱ ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት በማስረከብ ነው። ከተመላሾቹ መካከል ብርሃኑ አወቀ እና ስመኘው አዳነ፤ የተሳሳተ መንገድ ተከትለን በሕዝብ ላይ በፈጸምነው ጥፋት ተፀፅተናል ብለዋል። ግጭት በመፍጠር በአካባቢው ሕብረተሰብ በእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ ጫና ማሳደራችን ተገቢነት እንደሌላው ተገንዝበን ተመልሰናል ሲሉ ገልጸዋል። መንግስት ያመቻቸውን የሰላም እድል መምረጣቸውን ገልጸው፤ በጥፋታቸው በመፀፀት በቀጣይ በሰላም ግንባታና ልማት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህንንም ከመንግስትና ከሕብረተሰቡ ጎን በመሰለፍ በተግባር ለማረጋገጥ እንጥራለን ብለዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረሰ አዱኛ በበኩላቸው፤ ሰላምን ማፅናት ላይ ትኩረት ያደረጉ ሕዝባዊ ውይይቶች በተለያዩ የዞኑ አካባቢዎች ሲካሄዱ መቆየታቸውን ተናግረዋል። ከወይይቱ በኋላ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር ሕብረተሰቡ ድጋፉን ይበልጥ አጠናክሮ ሰላምን ለማፅናት በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መቻሉን ገልጸዋል። ወደ ሰላም የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችም የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ የቀሩትም እንዲመለሱ አሁንም የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል።
ወጣቶች የመደመር መንግስት እሳቤን እውን በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው
Dec 23, 2025 190
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ ወጣቶች የመደመር መንግስት እሳቤን እውን በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው የሲዳማ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። የሲዳማ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽንና ወጣቶቸ ማህበር “የተደመረ የወጣት አደረጃጀት ለሀገር ልማት እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ የምክክር ጉባኤ በሀዋሳ አካሂዷል። በጉባኤው የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ እመቤት ኢሳያስ እንዳሉት፤ ወጣቱ በክልሉም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት በሚደረገው ርብርብ ወጣቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል። ለዚህም በመደመር መንግስት እሳቤ የወጣቶችን አቅም በመገንባት ልማቱን ለማፋጠን ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል። የወጣቱን የስራ እድል ፈጠራ ለማሳደግም የክህሎት ስልጠናና የመስሪያና የመሸጫ እንዲሁም የብድር አገልግሎት አንዲያገኙ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የቢሮው ምክትልና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ለገሰ በበኩላቸው የክልሉ መንግስት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ የወጣቱን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማና በገጠር በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የወጣቱ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱንም ጠቁመዋል። የወጣቶች ፌዴሬሽንና ማህበር የጋራ ጉባኤው በመደመር እሳቤ ጠንካራ አደረጃጀት እንዲኖር ለማድረግና አመራሩን በአዲስ መልክ እንዲሰይም ታስቦ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። በጉባኤው የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆኖ የተመረጠው ወጣት ምንተስኖት መኩሪያ በበኩሉ ለሀገር ልማትና ሰላም ወጣቱ የነቃ የዜግነት ተሳትፎውን እንዲያሳድግ እንሰራለን ብሏል። በዚህም እንደ ወጣት ጠቃሚ ስራ በመስራት ለክልሉም ሆነ ለሀገር ብልጽግና ጉዞ መሳካት የድርሻውን ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን ጠቁሟል። የፌዴሬሽኑ አባል የሆነችው ወጣት ዘላለም ሰለሞን በበኩሏ የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንዲጎለብት ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስታውሳለች። ተግባሩንም በማስቀጠል ወጣቶች በሀገር ጉዳይ በንቃት እንዲሳተፉ በማስተባበር የበኩሏን እንደምትወጣም ገልጻለች። በጉባኤው የተለያዩ ክልሎች ፌዴሬሽን አመራሮች፣ ከሲዳማ ክልል አራት ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የወጣት ማህበራትና ፌዴሬሽን አደረጃጀቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።
የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላችንን እንወጣለን-የመተማ ወረዳ ነዋሪዎች
Dec 23, 2025 144
መተማ፤ ታህሳስ14/2018 (ኢዜአ):-የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ አስተዳደር ነዋሪዎች ተናገሩ። በመተማ ወረዳ ጉባይ ጀጀቢት ከተማ ዘላቂ ሰላም ግንባታን መሰረት ያደረገ ሕዝባዊ ውይይት ዛሬ ተካሄዷል። በውይይት መድረኩ ላይም ነዋሪዎቹ ፤ የአካቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ሙሉነህ ጥጋቡ ፤ በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም በማፅናት ልማት እንዲጠናከር የሚደግፉ መሆኑን ገልጸዋል። ሕግ የማስከበር ተግባር ተጠናክሮ የሰፈነውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል። ሌላኛው ተሳታፊ አቶ ክፍሌ ለጋስ ፤ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ለሁሉም ነገር ሰላም አስፈላጊ ነው ያሉት ቄስ አሰፋ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ መንግስት ለዘላቂ ሰላም እያደረገ ያለውን ተግባር እንደሚደግፉ አስታውቀዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፤ሕዝቡ በሰላም ማስከበር ተግባር የነቃ ተሳትፎውን ይበልጥ ማጠናከር ይኖርበታል። መንግስት ሰላምን ለማፅናት እያደረገ ያለው የሕግ ማስከበር ተግባር ውጤት እያመጣ መሆኑን አንስተዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረሰ አዱኛ፤ መንግስት ከሕግ ማስከበር ስራ ጎን ለጎን የሰላም አማራጭን ለሚቀበሉ በሆደ ሰፊነት አሁንም በሩን ከፍቷል ብለዋል። ሆኖም በሽፍትነት በመቀጠል ሕዝቡን ሰላም በሚነሱት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አረጋግጠዋል።
ፖለቲካ
የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ነው
Dec 25, 2025 88
ባሕርዳር ፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ) ፡- የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር፤ አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔ በባሕርዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፤ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በቅርቡ የተፈራረመው የዘላቂ ሰላም ስምምነት በክልሉ ሰላምን ለማፅናት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የክልሉ መንግስት ችግሮችን በውይይትና በንግግር መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲያቀርብ የነበረው የሰላም አማራጭ ፍሬ ማፍራቱን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል። ግጭት ይብቃ ብለው የክልሉን መንግስት የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለተመሰሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን ምክር ቤቱ ያመሰግናል ያሉት አፈ ጉባኤዋ ፤ ሌሎች በጫካ የቀሩ ታጣቂዎችም የሰላም ጥሪውን ተቀብለው እንዲመጡ ጠይቀዋል። የአማራ ክልል መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን ገልጸው ፤ አጠናክሮ እንዲቀጥል በምክር ቤቱ በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ትብብር የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክር ቤት አባላት ለመልካም አስተዳደር መስፈን፣ ለዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበርና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተያዘው ዓመት የሚካሄደው 7ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተአማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅና ህዝቡ በምርጫው በንቃት እንዲሳተፍ የምክር ቤት አባላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። ምክር ቤቱ የክልሉን ትምህርት ቢሮ የ5 ወራት እቅድ አፈፃፀምና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በተከናወኑ የፋይናንስ ህጋዊነትና ክዋኔ ኦዲት ግኝቶች ላይ እንደሚመክር ከመርሃ ግብሩ መረዳት ተችሏል። በጉባዔው ልዩ ልዩ አዋጆችና ሹመቶች እንደሚጸድቁም ይጠበቃል።
የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ ለውጦችን በሚያሳይ መልኩ ይከበራል
Dec 25, 2025 98
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ ከጥር 15 እስከ 19 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከበር በኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ ገለፁ። በበዓሉ ላይ "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በሚል የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብም ተመላክቷል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ፤ የአየር ኃይሉን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል መሪ ሃሳብ ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ደማቅ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር አስታውቀዋል። በበዓሉ ከጥር 15 ቀን ጀምሮ በሚካሄደውና "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በተሰኘው መርሃ ግብር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብ አመላክተዋል። በዚህም የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ የሩሲያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይሎች በጋራ በመሆን የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት እንደሚያቀርቡ ጠቅሰዋል። "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ የቻይና፣ ህንድ፣ አሜሪካ እና ደቡብ አፍሪካ ግዙፍ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ኤክስፖ እንደሚካሄድም ገልፀዋል። ከ25 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ የቴክኖሎጂ ተቋማት የደረሱበትን ደረጃ ለጉብኝት ክፍት የሚያደርጉበት "ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2026" እንደሚካሄድም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የአቪዬሽን ማዕከል መሆኗን የምታረጋግጥበት "ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም" ለሶስተኛ ጊዜ እንደሚካሄድም ተናግረዋል። "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው መድረክ ላይ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦችና ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች ይታደማሉ ነው ያሉት። የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አዛዦችና የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል ርዕስ ከህዝቡ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ጠቅሰዋል። በዓሉ የአየር ኃይሉን የ90 ዓመት የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በማሳየት ይከበራል ነው ያሉት። መላው የሀገሪቱ ህዝብ በዚህ ታሪካዊ በዓል ላይ በመገኘት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የደረሰበትን ዝግጁነት እንዲመለከት ጥሪ አቅርበዋል። የበዓሉ አካል የሆነና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ሃሳብ ባሳለፍነው ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ የ10 ኪሎ ሜትር ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ሩጫ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይህ ውድድር በህዝብና በተቋሙ መካከል ያለውን ትስስር ያጠናከረና ለዋናው በዓል መሰረት የጣለ ታሪካዊ ኹነት ሆኖ ማለፉንም ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
Dec 25, 2025 64
ባሕር ዳር፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔውን መካሄድ ጀምሯል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ የአምስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለጉባዔው ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል። በውይይቱ በትምህርት አጀማመርና በተከናወኑ ተግባራት ላይ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ተጠቁሟል። እንዲሁም በክልሉ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የፋይናንስ ሕጋዊነትና የክዋኔ ኦዲት ግኝቶችንና የተሰጡ የማሻሻያ ሐሳቦችን የሚያሳይ የተጠቃለለ ሪፖርት ላይ እንደሚመክር ተመላክቷል። ጉባዔው ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፤ በቆይታው ልዩ ልዩ ዐዋጆች እና ሹመቶችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።
መንግሥት ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል-የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Dec 24, 2025 159
አዲስ አበባ፣ታኅሣስ 15/2018(ኢዜአ)፡-መንግሥት የሀገር ግንባታ ሂደቱን ለማጽናት እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል፡፡ እነዚህ ሦስቱ ምሰሶዎች ሀገራዊ አንድነትን፣ሰላምና ብልጽግናን፣ እንዲሁም ዜጎች በመተማመን እና በተጠያቂነት ላይ የተመሠረተ የጋራ ራዕይ እንዲኖራቸዉ የሚያደርጉ ቁልፍ መሰረቶች ናቸው፡፡ ዲሞክራሲን የመገንባት ሂደት ለአንድ ሀገር ወሳኝ ተግባር ሲሆን፣ በዋናነት ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቁ ተቋማትን ማቋቋም ላይ ትኩረት ያደረገ ነዉ፡፡ተቋማቱ የሚመሩባቸዉ ህጎችና የአሰራር ሥርዓቶች፣የተቋማቱ አወቃቀርና አደረጃጀት፣ እንዲሁም ለህዝብ ያላቸዉን ተዓማኒነትን መጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራበት ይገኛል፡፡ ጠንካራ የዲሞክራሲ ባህልና ሥርዓት የሚገነባው ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት ሲፈጠሩና ሲጠናከሩ መሆኑን መንግሥት በጽኑ የሚገነዘበው ጉዳይ ነዉ፡፡በዚህም ኢትዮጵያ ባለፉት 7 ዓመታት በዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ሂደት ውስጥ ሁለተናዊ ሪፎርም ሥራዎችን ስታከናውን ቆይታለች፡፡ እነዚህ ሪፎርሞች የሀገሪቱን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑትን የዲሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እና ጠንካራ አድርጎ ለመገንባት መንግሥት ምን ያህል ቁርጠኛ እንደሆነ ያሳየባቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ተቋማት መጠናከር በአንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም እና ልማት እንዲረጋገጥ እንደ ዋንኛ ምሰሶ የሚወሰድ ነው፡፡ በተለይም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ የታዩ ተጨባጭ ለውጦች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ለመጠበቅ፣ እንዲሁም የሕዝቡን ዕምነት ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ መንግሥት በተለይ ተቋማዊ ዐቅምን በማሳደግ እና ነፃነትን በማረጋገጥ፣ የዲሞክራሲ ምህዳርን እንዲሰፋ ለማደረግ የሚጠበቅበት ግዴታ ብቻ ሳይሆን ዲሞክራሲ የሚያብብበትን አስቻይ ዐውድና ማዕቀፍ ለመፍጠር ዓለማው አድረጓል፡፡ ይሄንን ከግብ ለማድረስ በተለይ የፀጥታ፣ የፍትሕ፣ የሲቪልና የሚዲያ ተቋማት፣ እንዲሁም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕዝብን ማዕከል አድርገው እንዲሰሩ መንግሥት በቁርጠኝነት በመደገፉ እንደ ሀገር ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ በማደርረግ ተጨባጭ ዉጤቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል፡፡ ሌላው መንግስት በትኩረት እየሰራበት ያለው ጉዳይ እንደ ሀገር ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ነዉ፡፡ ይህ ሂደት ዋና ዓለማ ያደረገው መላዉ ሕዝብ፣ ተቋማት፣ አመራርና ሠራተኛዉ በሀገራዊ ራዕይ ላይ በተለያዩ ድምጾች የጋራ እድገትን በመገንባት ሀገራዊ ህለውና እና ብልጽግና እንዲረጋገጥ እንዲሁም በዜጎች መካከል መተማመን እና ሀገራዊ አንድነትን እንዲፈጠር ማድርግ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ የብዙሃን ድምጽ የሚሰማበት የፖለቲካ ዐዉድ ለመፍጠር አያሌ የፖለቲካ ማሻሻያዎችን አድርጋለች፡፡ በዚህም እስከዛሬ በነበሩ መንግሥታት ያለተሞከረውን ጫፍ ወጥተው የሚታዩ ተቃርኖ ሀሳቦችን ለማጥበብና ለማቀራረብ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም፣ ሀገራዊ የውይይት መድረክ እንዲፈጠር ተደርጓል፡፡ በዚህም ገና ከወዲሁ በርካታ ለዉጦች እየታዩ ሲሆን ውሳኔው ለምንመኛት የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን የማዕዘን ድንጋይ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ በአጠቃላይ መንግሥት መልአተ ሕዝቡን በማስተባበር ጠንካራና ብልጽግናዋን በልጆቿ ያረጋገጠች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እያደረገ ባለው ዘርፈ ብዙ ጥረት ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን የመፍጠርን ጉዳይ በልዩ ትኩረት የሚሰራበት ዋንኛው አጀንዳው ሆኖ ይቀጠላል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ
Dec 24, 2025 198
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 15/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ ገጽ ይፋ ሆኗል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን የዝግጅትን በ etaf90years.com ድረ-ገፅ አማካኝነት አጠቃላይ መረጃ ማግኘት እንደሚቻል ተቋሙ አስታውቋል። የምስረታ ቀን በዓሉ ላይ ኅብረተሰቡ እንዲሳተፍም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባወጣው መግለጫ ገልጿል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓሉን አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል:- ነሐሴ 12 ቀን 1921 ዓ.ም የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ የገባ ቢሆንም አየር ኃይላችን እንደ ተቋም አደረጃጀት ይዞ በይፋ የተመሰረተው ሕዳር 20 ቀን 1928 ዓ.ም ኢትዮጵያዊው ሻለቃ ሚሽካ ባብቼፍ የአየር ኃይል አዛዥ ሆነው በተመደቡበት ቀን ነው፡፡ ጀግናው የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90 ዓመታትን ባስቆጠረው የምስረታ ታሪኩ በየዘመናቱ ሁሉ የሀገርን ሉዓላዊነት በመጠበቅ አኩሪ ታሪክ ያለው ስመ ገናና ተቋም ነው፡፡አየር ኃይላችን የኢትዮጵያን የአየር ክልል በጀግንነት ከመጠበቅ ባሻገር በዓለም አቀፍ የሠላም ማስከበር ተልዕኮዎች በመሰማራት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ አውለብልቧል፡፡ የሠላም አምባሳደርነቱንም በተግባር አሳይቷል፡፡ በድል እና በመስዋዕትነት የደመቀ ታሪክም አኑሯል፡፡ በስልጠናው ዘርፍም ከራሱ አልፎ የሌሎች ሀገራት የአየር ኃይል ሙያተኞችን ማሰልጠኑን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ 90ኛ ዓመት የአየር ኃይል የምስረታ ቀን በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል ዋና መሪ ቃል ከጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድርስ በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድምቀት ይከበራል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር የጀመረ ሲሆን የዚሁ አካል የሆነውና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ቃል ሕዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ዓለም አቀፍ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በድምቀት ተካሂዷል፡፡ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ታላቅ አየር ኃይል እየተገነባ ነው -ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ይህ የሩጫ ውድድር ህብረተሰቡ በከፍተኛ መነቃቃት የተሳተፈበት፣ ተቋሙና ህዝቡ የተሳሰረበት፣የቱሪስት መዳረሻ የሆነችው ቢሾፍቱ ከተማ የተዋወቀችበት ከመሆኑም ባሻገር በቀጣይ ለሚካሄዱት ኩነቶች የአየር ኃይል የምስረታ ቀን ዋናው በዓል መሰረት ጥሎ ያለፈ ታሪካዊ ውድድር ነው፡፡ በመቀጠል ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ዓ.ም ጀምሮ የሚኖረው የሚከተሉትን ኩነቶች የያዘ ነው የመጀመሪያው በዓይነቱ ለየት ያለ እና ለሁለተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አየር ኃይል አዘጋጅነት ‘የአንበሶች ሠማይ! ኢትዮጵያ’ በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአየር ኃይል፣ የሩሽያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ የአየር ኃይል እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይል በጋራ የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት 2026 በድምቀት የሚካሄድ ይሆናል፡፡ በመቀጠል በከፍተኛ ጉጉት የሚጠበቀው "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የቻይና፣ የህንድ የአሜሪካ እና የደቡብ አፍሪካ ታላላቅ ኩባንያዎች ብሎም ከ 25 በላይ የሚሆኑ በአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት የአቪዬሽንና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ2026 ይካሄዳል፡፡ የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓል ከሚያከናውናቸው ኩነቶች አንዱ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦች የሚሳተፉበት እና "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ለ3ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አየር ኃይል አዘጋጅነት ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች በተገኙበት የሚካሄድ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ ከአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ጋር ያላትን ቅርብ ትስስር በተግባር የሚያረጋግጥ ይሆናል፡፡ አየር ኃይል የሀገርን ሉዓላዊነት በማስከበር አኩሪ ታሪክ አለው- ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓል ከሚካሄዱ መርሃ ግብሮች መካከል የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ የጦር አዛዦች እንዲሁም የሀገራችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል መሪ ቃል ከህብረተሰቡ ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ሕዝባዊ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ የበዓሉን የአከባበርን ሁኔታ የሚገልፅ እና የአየር ኃይልን ታሪክ የበለጠ የሚያሳውቅ፣ የዝግጅቱን ዝርዝር የሚያሳይ እንዲሁም የባለፉት ዓመታትን የተቋሙን የለውጥ ሂደት የሚያስቃኝና etaf90years.com የተሰኘ የኢቨንት ድረ ገፅ ያለው ሲሆን በዚሁ ድህረ ገፅ ሁሉንም የበዓሉ ኩነቶች ማግኘት የመግቢያ ቲኬት መግዛትና በድረ ገፅ ኩነቶቹን መከታተል ይቻላል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል በ90 ዓመት ጉዞው ለኢትዮጵያችን መስዋዕትነት ከፍሏል፡፡ የኢትዮጵያን የአየር ክልል በጀግንነት ጠብቋል፡፡ ሀገር አፅንቷል፤ ሀገር አሻግሯል፡፡ በእሳት ተፈትነው ያለፉ ብዙ ጀግኖችንም አፍርቷል፡፡ በውጊያ መሰረተ ልማት፣በሰው ኃይል ግንባታና ትጥቅ በማሟላት ኢትዮጵያን የሚመጥን ተቋም እየተገነባ ነው የከበረ እና የገዘፈ ታሪክ ያለው የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓሉን ሲያከብርም ያለፈውን ለመዘከር አሁናዊ የተቋሙን ቁመና ለማቀብ፣ የደረሰበትን ሁሉን አቀፍ ዝግጁነት ለማሳየት፣ የሀገራችንን ገጽታ በማጉላት እና የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ተስፋ ለማነሳሳት በሚያስችሉ ዝግጅቶች እንዲሁም ተግባራት የሚከበር መሆኑ ተመላክቷል። ኅብረተሰቡ በዓሉ ላይ እንዲገኝና በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባል ሆነው ያገለገሉትንና እያገለገሉ ያሉ ጀግኖችን እንዲያከብር፣ እንዲዘክር፣ የሀገር መመኪያና ኩራት የሆነው ተቋም እንዲመለከትና በዚህ አስደናቂና ታሪካዊ በዓል ላይ እንዲታደም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጥሪውን አቅርቧል፡፡
ልማት ላይ በመሳተፍ የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል - የቀድሞ ታጣቂዎች
Dec 24, 2025 169
መተማ፤ ታህሳስ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በሰላም ግንባታና ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል ሲሉ በምዕራብ ጎንደር ዞን የሰላም አማራጭን ተቀብለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች ገለጹ። በዞኑ መተማ ወረዳ ጉባይና ሌንጫ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ታጣቂዎቹ የሰላምን አማራጭ ተቀብለው ሲመለሱ ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት በማስረከብ ነው። ከተመላሾቹ መካከል ብርሃኑ አወቀ እና ስመኘው አዳነ፤ የተሳሳተ መንገድ ተከትለን በሕዝብ ላይ በፈጸምነው ጥፋት ተፀፅተናል ብለዋል። ግጭት በመፍጠር በአካባቢው ሕብረተሰብ በእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ ጫና ማሳደራችን ተገቢነት እንደሌላው ተገንዝበን ተመልሰናል ሲሉ ገልጸዋል። መንግስት ያመቻቸውን የሰላም እድል መምረጣቸውን ገልጸው፤ በጥፋታቸው በመፀፀት በቀጣይ በሰላም ግንባታና ልማት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህንንም ከመንግስትና ከሕብረተሰቡ ጎን በመሰለፍ በተግባር ለማረጋገጥ እንጥራለን ብለዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረሰ አዱኛ በበኩላቸው፤ ሰላምን ማፅናት ላይ ትኩረት ያደረጉ ሕዝባዊ ውይይቶች በተለያዩ የዞኑ አካባቢዎች ሲካሄዱ መቆየታቸውን ተናግረዋል። ከወይይቱ በኋላ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር ሕብረተሰቡ ድጋፉን ይበልጥ አጠናክሮ ሰላምን ለማፅናት በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መቻሉን ገልጸዋል። ወደ ሰላም የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችም የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ የቀሩትም እንዲመለሱ አሁንም የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል።
ወጣቶች የመደመር መንግስት እሳቤን እውን በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው
Dec 23, 2025 190
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ ወጣቶች የመደመር መንግስት እሳቤን እውን በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው የሲዳማ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። የሲዳማ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽንና ወጣቶቸ ማህበር “የተደመረ የወጣት አደረጃጀት ለሀገር ልማት እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ የምክክር ጉባኤ በሀዋሳ አካሂዷል። በጉባኤው የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ እመቤት ኢሳያስ እንዳሉት፤ ወጣቱ በክልሉም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት በሚደረገው ርብርብ ወጣቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል። ለዚህም በመደመር መንግስት እሳቤ የወጣቶችን አቅም በመገንባት ልማቱን ለማፋጠን ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል። የወጣቱን የስራ እድል ፈጠራ ለማሳደግም የክህሎት ስልጠናና የመስሪያና የመሸጫ እንዲሁም የብድር አገልግሎት አንዲያገኙ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የቢሮው ምክትልና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ለገሰ በበኩላቸው የክልሉ መንግስት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ የወጣቱን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማና በገጠር በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የወጣቱ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱንም ጠቁመዋል። የወጣቶች ፌዴሬሽንና ማህበር የጋራ ጉባኤው በመደመር እሳቤ ጠንካራ አደረጃጀት እንዲኖር ለማድረግና አመራሩን በአዲስ መልክ እንዲሰይም ታስቦ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። በጉባኤው የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆኖ የተመረጠው ወጣት ምንተስኖት መኩሪያ በበኩሉ ለሀገር ልማትና ሰላም ወጣቱ የነቃ የዜግነት ተሳትፎውን እንዲያሳድግ እንሰራለን ብሏል። በዚህም እንደ ወጣት ጠቃሚ ስራ በመስራት ለክልሉም ሆነ ለሀገር ብልጽግና ጉዞ መሳካት የድርሻውን ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን ጠቁሟል። የፌዴሬሽኑ አባል የሆነችው ወጣት ዘላለም ሰለሞን በበኩሏ የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንዲጎለብት ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስታውሳለች። ተግባሩንም በማስቀጠል ወጣቶች በሀገር ጉዳይ በንቃት እንዲሳተፉ በማስተባበር የበኩሏን እንደምትወጣም ገልጻለች። በጉባኤው የተለያዩ ክልሎች ፌዴሬሽን አመራሮች፣ ከሲዳማ ክልል አራት ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የወጣት ማህበራትና ፌዴሬሽን አደረጃጀቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።
የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላችንን እንወጣለን-የመተማ ወረዳ ነዋሪዎች
Dec 23, 2025 144
መተማ፤ ታህሳስ14/2018 (ኢዜአ):-የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ አስተዳደር ነዋሪዎች ተናገሩ። በመተማ ወረዳ ጉባይ ጀጀቢት ከተማ ዘላቂ ሰላም ግንባታን መሰረት ያደረገ ሕዝባዊ ውይይት ዛሬ ተካሄዷል። በውይይት መድረኩ ላይም ነዋሪዎቹ ፤ የአካቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ ለሕግ የበላይነት መከበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ሙሉነህ ጥጋቡ ፤ በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም በማፅናት ልማት እንዲጠናከር የሚደግፉ መሆኑን ገልጸዋል። ሕግ የማስከበር ተግባር ተጠናክሮ የሰፈነውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል። ሌላኛው ተሳታፊ አቶ ክፍሌ ለጋስ ፤ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የአካባቢያቸውን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ለሁሉም ነገር ሰላም አስፈላጊ ነው ያሉት ቄስ አሰፋ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ መንግስት ለዘላቂ ሰላም እያደረገ ያለውን ተግባር እንደሚደግፉ አስታውቀዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፤ሕዝቡ በሰላም ማስከበር ተግባር የነቃ ተሳትፎውን ይበልጥ ማጠናከር ይኖርበታል። መንግስት ሰላምን ለማፅናት እያደረገ ያለው የሕግ ማስከበር ተግባር ውጤት እያመጣ መሆኑን አንስተዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረሰ አዱኛ፤ መንግስት ከሕግ ማስከበር ስራ ጎን ለጎን የሰላም አማራጭን ለሚቀበሉ በሆደ ሰፊነት አሁንም በሩን ከፍቷል ብለዋል። ሆኖም በሽፍትነት በመቀጠል ሕዝቡን ሰላም በሚነሱት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አረጋግጠዋል።
ማህበራዊ
ትህነግ ሕዝብን በርሃብ በመቅጣት ለፖለቲካ መሳሪያነት የመጠቀም ተግባሩን ዳግም በትግራይ ህዝብ ላይ እያሳየ ነው
Dec 25, 2025 23
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 16/2018(ኢዜአ)፦ ትህነግ ሕዝብን በርሃብ በመቅጣት ለፖለቲካ መሳሪያነት የመጠቀም ተግባሩን ዳግም በትግራይ ሕዝብ ላይ እያሳየ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽነር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) ተናገሩ። የትህነግ ቡድን የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል በመጠለያ ማዕከላትና በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር የሚያቀርበውን ሰብዓዊ ድጋፍ ለተፈለገው ዓላማ እንዳይውል እያደረገ እንደሚገኝም የሰሞኑ የህፃፅ መጠለያ ጣቢያ ማስረጃ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የትህነግ ህገወጥ ቡድን የትግራይን ሕዝብ መሠረታዊ ፍላጎቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች ለፖለቲካ ዓላማ የመጠቀም ልማድ አዲስ ክስተት ሳይሆን የቀደመ ታሪኩና መገለጫው ነው። ትህነግ የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ለመሳብ በትግራይ ክልል በመጠለያ ጣቢያዎች ለሚገኙ ወገኖች የሚቀርብን ሰብዓዊ ድጋፍ በመንጠቅ ድራማዊ ፕሮፓጋንዳ እያስተጋባ መሆኑንም አስረድተዋል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም የፌደራል መንግስት በግልጽ መረጃና ማስረጃ የሚልከው ሰብዓዊ ድጋፍ የት እንደገባ መጠየቅ እንዳለበት እና በቡድኑ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ መደናገር እንደሌለበትም አንስተዋል። ትህነግ ሰብዓዊ ድጋፍ ለፖለቲካ ዓላማ ለማዋል የሚያደርገውን ጥረት ሁሉም ሊገነዘበው እንደሚገባም ጠቅሰዋል። የፌደራል መንግስትም በትግራይ ክልል አስተማማኝና ቀጣይነት ያለው ሰብዓዊ ድጋፍ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በዚህም በትግራይ ክልል ከባለፈው ጥር 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታኅሳስ ወር 2018 ዓ.ም ድረስ ሁለት ሚሊየን ኩንታል በገንዘብ ሲተምን 32 ቢሊዮን ብር የሚገመት ሰብዓዊ ድጋፍ መሰራጨቱን አስታውቀዋል። ይህም የፌደራል መንግስት ዜጎች ሰብዓዊ ጉዳት እንዳይደርስባቸው ያለውን ጠንካራ አቋም በተግባር የሚያረጋግጥ መሆኑንም ነው ያብራሩት። የትህነግ ቡድን በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፉ ተደራሽ እንዳይሆን በማስተጓጎል፤ ድጋፉን ከችግረኛ ዜጎች በመንጠቅ ዳግም የሕዝብ ጠላትነቱን እያረጋገጠ እንደሚገኝም አብራርተዋል። ቡድኑ ይህ አልበቃ ብሎት ለእያንዳንዱ ድጋፍ ፈላጊ ዜጋ ከሚሰጥ የፍጆታ ድርሻ ላይ መዋጮ እንደሚሰበስብም ነው የተናገሩት። ትህነግ በሰብዓዊ ድጋፍ ስም በዜጎች ላይ የሚፈጽመው አስነዋሪ ድርጊት ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ያለውን የተላላኪነት ጥግ በተግባር ያረጋገጠ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ኮሚሽኑ የድጋፍ ጥሪ ባላቀረበበት ሁኔታ በማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች በቡድንም ሆነ በተናጠል የሚደረጉ የድጋፍ ማሰባሰብ ዘመቻ የአሰራር ስርዓትን የጣሱ ህገ-ወጥ አካሄዶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በዚህም የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም ሰብዓዊ ድጋፍ በማሰባሰብ ላልተገባ ዓላማ እያዋሉ የሚገኙ አካላት ከድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በክልሉ የመማር ማስተማር ስራ ቅድሚያ የሚሰጠው ቁልፍ የልማት ተግባር ሆኖ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Dec 25, 2025 42
ባህር ዳር፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥና ተደራሽነትን ማስፋት ቅድሚያ የሚሰጠው ቁልፍ የልማት ተግባር ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ አረጋ ከበደ ለምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ እንዳሉት፤ የትምህርት ዘርፉ ከልማቶች ሁሉ ቅድሚያ የሚሰጠው የዘላቂ እድገት አቅም ነው። በመሆኑም በክልሉ የመማር ማስተማር ስራው ቅድሚያ የሚሰጠው ቁልፍ የልማት ተግባር ሆኖ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ የተስተዋለው የሰላም መታጣት ችግር በመማር መስተማር ስራው ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩን ጠቅሰው፤ ችግሩን በመቋቋም የተሰራው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ገልፀዋል። አሁንም የመማር ማስተማር ስራውንም ሆነ ሌሎች የልማት ስራዎችን የበለጠ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሰላምን በዘላቂነት የማስፈኑ ስራ በተጀመረው አግባብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ለመማር ማስተማር የሚያግዙ ግብዓቶችን በማሟላት፣ ከደረጃ በታች የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል፣ በቴክኖሎጂ የታገዙ አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን በመገንባትና መሰል ለትምህርት ጥራት እንዲሁም ተደራሽነት የሚያግዙ ተግባራት ከየትኛውም ልማት ቅድሚያ ተሰጥቷቸው ይከናወናሉ ብለዋል። የትምህርት ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ሁሉ እገዛና ትብብር በማድረግ የትምህርት ተቋማትን በባለቤትነት በመገንባትና ግብዓት በማሟላት የሚጠበቅበትን ሚና ሁሉ ሊወጣ እንደሚገባም አሳስበዋል። የትምህርት ቤት ምገባ ለትምህርት ሽፋን ማደግና ጥራት መረጋገጥ እያገዘ መሆኑን ጠቅሰው፤ አሁንም የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ ከመንግስት ባለፈ ባለሃብቱና ማህበረሰቡ በንቅናቄ ሊሰራው ይገባል ብለዋል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ በበኩላቸው፤ ለመማር መስተማር ስራው የሚያግዙ ግብዓቶችን በተቻለ አቅም ለማሟላት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። ተደራሽነትን ለማረጋገጥም የ63 ትምህርት ቤቶች ግንባታ መጀመሩን ጠቅሰው፤ ማህበረሰቡን በማስተባበር በራሱ አቅም ትምህርት ቤቶችን ገንብቶ ለአገልግሎት እንዲያበቃ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል። በአሰራር የሚስተዋሉ ክፍተቶችንና የግብዓት አለመሟላትን በጥናት ላይ መሰረት ያደረገ ምላሽ ለመስጠትም ቡድን ተዋቅሮ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። ምክር ቤቱ የክልሉን የ5 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ከገመገመ በኋላ ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጡም ተመልክቷል።
በክልሉ የመማር ማስተማር ስራውን ይበልጥ ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Dec 25, 2025 42
ባሕርዳር፤ ታሕሳስ 16/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የመማር ማስተማር ስራውን ይበልጥ ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ። የአማራ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር፣ አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔ እየተካሄደ ነው። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ነው የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ጥላሁን ወርቅነህ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳመለከቱት፤ በክልሉ በትምህርት ዘመኑ ከቅድመ አንደኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ከ7 ሚሊየን በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል። ይህንኑ የመማር ማስተማር ስራን ይበልጥ ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸው፤ በመማር ላይ የሚገኙት ተማሪዎች ቁጥር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል። ለመማር ማስተማር ስራው ከ36 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ የመማሪያና የማስተማሪያ መፅሐፍት ታትመው መሰራጨታቸውን ገልጸዋል። በአንድ ሺህ 107 ትምህርት ቤቶች 255ሺህ 367 ተማሪዎችን ተጠቃሚ ያደረገ የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር እየተከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በተጨማሪም 157 ትምህርት ቤቶችን በአዲስ በመገንባት፣ ሁለት ሺህ 468 ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን እና ከ13ሺህ 800 የሚበልጡ ነባር የመማሪያ ክፍሎችን በመጠገን ለአገልግሎት መብቃታቸውንም አብራርተዋል። የክልሉን የትምህርት ስራ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ እየተከናወኑ በሚገኙት ተግባራት ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ለምክር ቤቱ በቀረበው የክልሉ የ2018 የትምህርት ዘመን 5 ወራት የትምህርት አፈፃፀም ሪፖርት ዙሪያ ምክክር እየተደረገ ይገኛል።
አካል ጉዳተኞችን በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተደርጓል
Dec 25, 2025 61
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡- አካል ጉዳተኞችን በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ የክህሎት አቅማችውን እንዲያሳድጉ ትኩረት መደረጉን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና ልማት ማዕከል ጋር በመተባበር የአካል ጉዳተኞች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የአካቶ መመሪያ የትውውቅ መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና ልማት ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ስምኦን (ዶ/ር) ፤ ከክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ አካል ጉዳተኛ ወገኖች በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ተሰማርተው ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ከመጥቀም ባለፈ ሀገራቸውን እያገለገሉ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በአካል ጉዳተኞች የሚመሩ ግዙፍ ተቋማት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህን ወገኞች በክህሎት ልማት ማብቃት ከተቻለ የበለጠ ምርታማ መሆን እንደሚችሉ ተናግረዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አካል ጉዳተኞችን በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ማድረጉን ገልጸዋል። ከዚህ በፊት አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረገ ሀገር አቀፍ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ተቀርጾ ተግባራዊ መደረጉን አስታውሰዋል። የመድረኩ ዋና ዓላማ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂን መሰረት በማድረግ በተዘጋጀው የአካል ጉዳተኞች የአካቶ ትምህርት መመሪያ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ለመምከር መሆኑን አመላክተዋል። አዲሱ መመሪያ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የአካቶ ትምህርት ተደራሽነትን፣ ክብር ያለው የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር የስራ ስምሪትንና ምቹ የስራ ቦታ መፍጠርን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አመላክተዋል። መመሪያው በፍጥነት ተግባራዊ እንዲደረግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና ልማት ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ስምኦን(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መንግስት ለአካል ጉዳተኞች የሰጠው ትኩረት የሚደነቅ ነው ብለዋል። በተለይም አካል ጉዳተኞችን በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የተሰራው ስራ በርካታ ወገኖችን ስኬታማ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። አዲሱ መመሪያም አካል ጉዳተኞች በእውቀት ላይ የተመሠረተ ተግባር እንዲያከናውኑ በማድረግ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ኢኮኖሚ
በእንስሳት ሃብት ልማት የአርሶ አደሮችን ምርታማነትና ዘላቂ ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Dec 25, 2025 33
ባቱ፤ ታህሳስ 16/2018(ኢዜአ)፦ በእንስሳት ሃብት ልማት የአርሶ አደሮችን ምርታማነትና ዘላቂ ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። ምርታማነታቸውና ውጤታማነታቸው የተረጋገጠ የተሻሻሉ የላም ዝርያዎች በምስራቅ ሸዋ ዞን ለሚገኙ አርሶ አደሮች ተላልፈዋል። በመርሃ ግብሩ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሣ(ዶ/ር)፤ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን ለአርሶ አደሮች ተደራሽ በማድረግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዘንድሮው ዓመት ብቻ 5 ሚሊየን የወተት ላሞችን ለማዳቀል ታቅዶ እስካሁን 2 ሚሊየን ማዳቀል መቻሉን ጠቅሰው በዘርፉ ልማት በትኩረት በመስራት የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን ከማሳደግ አንፃር በዶሮና የዓሣ ልማት እንዲሁም የንብ ማነብ ዘርፎች ላይ ተመሳሳይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በኦሮሚያ ክልል የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በዝሪያ ማሻሻያ ላይ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ ጌቱ ገመቹ ናቸው። ባለፈው ዓመት በክልሉ 2 ነጥብ 6 ሚሊየን ላሞችን በማዳቀል ከ400 ሺህ በላይ ዝርያቸው የተሻሻሉ ጥጆች መወለዳቸውን አንስተዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም ላሞችን በሰው ሰራሽና በመደበኛ የማዳቀል ስራ በብዛት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም የዘርፉን ልማትና ተጠቃሚነት የማሳደግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው የዛሬው መርሃ ግብርም የዚሁ ጥረት አካል ነው ብለዋል። የምስራቅ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አባቡ ዋቆ፤ በዞኑ በተለይም የሌማት ትሩፋትን በማስፋፋትና ሌሎች የልማት ስራዎችን አቀናጅቶ በመስራት ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮው ዓመት በዞኑ ከ59ሺህ በላይ ሰዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን አንስተው የእስካሁኑ ሂደት ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ ከእንስሳት ሃብት ልማት በተጨማሪ በበጋ መስኖ ስንዴ፤ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በሌሎች የሰብል አይነቶች ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት እንዲችሉ ትኩረት ተደርጓል
Dec 25, 2025 33
ጎንደር፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ) ፡-በአማራ ክልል የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት እንዲችሉ ትኩረት መደረጉን የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና በጎንደር ከተማ ዛሬ አስጀምሯል፡፡ የቢሮው ኃላፊ ስብሁ ገበያው (ዶ/ር) በስልጠና ማስጀመሪያው ላይ እንደገለጹት አዲሱ የስልጠና ፖሊሲና ስትራቲጂ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ገበያው የሚፈልገውን የሰው ኃይል በማምረት ላይ እንዲያተኩሩ የሚያስችል ነው። ስልጠናው ፖሊሲና ስትራቴጂው በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ ተመስርቶ ሀገር በቀል እውቀትን ማጎልበት ላይ እንዲያተኩር በማድረግ ወጣቱን ትውልድ መጥቀም ዓላማው ያደረገ ነው ብለዋል። የአለም ሀገራት እድገትና ብልጽግናቸውን ማረጋገጥ የቻሉት በመካከለኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሃይል ማፍራት ላይ በመስራታቸው ነው ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው፡፡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ኢኮኖሚውን የሚደግፉና ሀገር ገንቢ ትውልድ የሚያፈሩ በመሆናቸው የከተማ አስተዳደሩ ድጋፍና ትብብር በማድረግ ተቋማቱን የማጠናከር ስራ እንደሚሰራም አመልክተዋል። የጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተስፋሁን መኮንን በበኩላቸው አዲሱ ፖሊሲና ስትራቴጂ ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ለትምህርትና ስልጠና ጥራት መረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ለተግባር ልምምድ ልዩ ትኩረት የሰጠና አለም አቀፍ ሁኔታዎችን ባገናዘበ መንገድ በገበያ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል። ኮሌጁ በየዓመቱ ከሶስት ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ገበያ ተኮር በሆኑ የሙያ መስኮች አሰልጥኖ በማብቃት አምራች ኢንዱስትሪውን እየደገፈ እንደሚገኝም ገልጸዋል። ለአራት ቀናት በሚቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ላይም የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ከጎንደር ከተማ፣ ከማእከላዊና ከሰሜን ጎንደር ዞኖች የተውጣጡ የመንግስትና የግል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ዲኖች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
የሻሸመኔ ከተማ የኮሪደርና የመንገድ መሰረተ ልማት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴን ለማፋጠን አግዟል-ነዋሪዎች
Dec 25, 2025 91
ሻሸመኔ፤ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የሻሸመኔ ከተማ የኮሪደርና የመንገድ መሰረተ ልማት የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማፋጠን ማገዙን ነዋሪዎች ገለጹ። በከተማዋ ከ5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ከ26 ኪሎ ሜትር በላይ የተቀናጀ የኮሪደር ልማትና የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑም ተመላክቷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቭ በኢትዮጵያ ከተሞች ጽዱ፣ ለኑሮ ምቹና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ታስቦ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በተለያዩ ከተሞች እየተተገበረ ነው። ልማቱ ተግባራዊ ከሆነባቸው የሀገራችን ከተሞች አንዷ ሻሸመኔ ስትሆን በአስተዳደሩና በነዋሪው ትብብር እየተከናወነ ባለው የተቀናጀ የኮሪደርና የመንገድ መሰረተ ልማትም ከተማዋ እየደመቀች ነው። የልማት ሥራው የነዋሪውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማሳለጥ የከተማዋን ዕድገት ከማፋጠን ባለፈ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል። ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ከድር ገለቶ፣ ወይዘሮ በሻዬ ኤዶ እና አቶ ከድር አማን እንዳሉት፥ በከተማዋ የሚከናወኑት የልማት ስራዎች አዝጋሚ የነበረውን የከተማዋ እድገት የቀየሩና የነዋሪውን የልማት ጥያቄዎች የመለሱ ናቸው። በተለይ የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማዋን ለኑሮ ምቹና ለስራ ተመራጭ እያደረጋት መምጣቱን ገልጸዋል። የኮሪደር ልማቱ ምቹ የእግረኛና የተሽከርካሪ መንገዶች ማካተቱ የትራፊክ መጨናነቅን እያስቀረ መሆኑንም ጠቁመዋል። የከተማዋ ልማት ካላት ሰላም ጋር ተዳምሮ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዲፋጠኑ በማድረጉ ለሥራ ዕድል ማገዙንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። በኮሪደር ልማቱ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው መካከል አቶ ደጀኔ ስሜ ሰርተው በሚያገኙት ገቢ ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን እያስተዳደሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። በከተማዋ ከ5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት ከ26 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማትና የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ግንባታ ሥራ እየተፋጠነ ነው ያሉት ደግሞ የአስተዳደሩ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዲሳ ገመቹ ናቸው። የኮሪደር ልማትን ጨምሮ አጠቃላይ የከተማዋ የመሰረተ ልማት ሥራ ውበትና ገጽታን ከመቀየር ባለፈ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማፋጠን የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት እያሳደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በከተማዋ የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን በማስፋት ከተማዋን ተመራጭ፣ ተወዳዳሪና ምቹ የማድረግ ሥራው ይጠናከራል ያሉት ሥራ አስኪያጁ፣ የህዝብን የልማት ተሳትፎ በማጠናከር እስከ መጪው ግንቦት ወር ድረስ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል። የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አዳነ ተክለጊዮርጊስ በበኩላቸው፥ በከተማዋ ከዚህ ቀደም የነበረው የመንገድ ዝርጋታ ለሰውና ለተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ምቹ እንዳልነበር አንስተዋል። አሁን እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትና የአስፓልት መንገድ ግንባታ እነዚህን ችግሮች ከመፍታት ባለፈ ከተማዋን ዘመናዊና ተመራጭ በማድረግ የነዋሪውን ተጠቃሚነት ያሳድጋል ብለዋል። በከተማዋ ኮሪደርን ጨምሮ እየተከናወኑ ያሉት መሰረተ ልማቶች ሲጠናቀቁ በነዋሪው ህይወት ላይ ከፍተኛ መሻሻል እንደሚያመጡ የጠቀሱት ከንቲባው፣ ልማቱ በተያዘው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅም ልዩ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሻሸመኔ ከተማ ነዋሪዎች ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ስኬታማነት በሀሳብና በተግባር እያደረጉት ላለው ያላሰለሰ ትብብርና ድጋፍም ከንቲባው አመስግነዋል።
ቡና አምራች አርሶ አደሮችን ከኢንዱስትሪዎች ጋር በማስተሳሰር ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው
Dec 25, 2025 70
ሀዋሳ ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ከ200 ሺህ በላይ የሚሆኑ ቡና አምራች አርሶ አደሮችን ከኢንዱስትሪዎች ጋር በማስተሳሰር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝ የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፡ በክልሉ የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ በተሰሩ ስራዎች ዘርፈ ብዙ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው። በዚህም ከ200 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን ቡና አጥበውና ፈልፍለው ከሚያዘጋጁ ኢንዱስትሪዎች ጋር በማስተሳሰር የቡና ጥራትንና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከኢንዱስትሪዎች ጋር የተፈጠረውን ትስስር ከቡና ጥራት ባሻገር አርሶ አደሩ ከምርቱ ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኝ እያስቻለ መሆኑን ጠቁመው ባለፈው ዓመት 10 ኢንዱስትሪዎች ትርፍ ክፍፍል ማድረጋቸውንም ገልጸዋል፡፡ በክልሉ በንሳ ወረዳ ትስስር ከፈጠሩ አርሶ አደሮች ቡና የሚረከቡ ባለሃብቶች ፤ ትስስሩ ጥራትንና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም አርሶ አደሩ ከችግኝ ተከላ እስከ ቡና ለቀማ የባለሙያ ድጋፍ እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑንም አክለዋል፡፡ ለኢንዱሰትሪዎች ቡና ከሚያቀርቡ አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር አስፋው ሆሼ፤ ከተከላ ጀምሮ እስከ ቡና ለቀማ የባለሙያዎችን ምክር ተቀብለው በመስራታቸው የተሻለ ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ ከደረሰ ማሳቸው የለቀሙትን ከ220 ኪሎ ግራም በላይ ቡና ትስስር ለፈጠሩት ኢንዱስትሪ በማቅረብ በተገቢው ዋጋ መሸጣቸውን ተናግረዋል፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አስተዳደሩ ዲጂታል ማንነትን መሰረት ያደረገ ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የተሟላ ሥርዓት እየዘረጋ ነው
Dec 25, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 16/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲጂታል ማንነትን መሰረት ያደረገ ዘመናዊ አገልግሎት አሰጣጥን ማሳለጥ የሚያስችል የተሟላ ሥርዓት እየዘረጋ መሆኑን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትግበራን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት፤ ዲጂታል 2030 ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን መገንባት ቁልፍ የስትራቴጂው ግቦች እንደሆኑ አስረድተዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ አስተዳደሩ የሚሰጣቸው የመንግስት አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግ ሰፋፊ ስራዎችን በማከናወን ላይ ነው። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በፈጠረው መደላድልም ተቋማትን የማገናኝትና እንዲናበቡ የማድረግ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በተጨማሪም በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል በማዘጋጀትም የተገልጋዩን የአገልግሎት እርካታ ማሳደግ የሚያስችል አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀቱን አብራርተዋል። በመሆኑም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በመዲናዋ በሁሉም ተቋማት ዲጂታል ማንነትን ማሰረት ያደረጉ አገልግሎቶች የሚሰጡበት የተሟላ ስርዓት እየተዘረጋ መሆኑን ነው የገለጹት። ከተማ አስተዳደሩ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አኳያ ራሱን በመቃኘት የነዋሪዎችን የዲጂታል መታወቂያ መረጃን የማዋሀድ ስራ እንደሚሰራም ነው የጠቀሱት። በመዲናዋ የተለያዩ ተቋማት በሚሰጡ የኤሌክትሮኒክ አገልግሎቶች ነዋሪው ባለበት ሆኖ የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ በማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው የገለጹት። በዋናነትም የሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎትም ከፋይዳ መታወቂያ ጋር እንዲያያዝ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት መደላድል መፈጠሩን አብራርተዋል። የስማርት ሲቲ መገለጫ ዲጂታል አገልግሎትን በተሟላ መልኩ መስጠት ነው ያሉት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ የነዋሪነትና የሲቪል ምዝገባ ስርዓቱ ፍትሐዊ፣ ተጠያቂነት ያለበት፣ ተደራሽና ዘመናዊ ለማድረግም እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በዘንድሮው በጀት ዓመት ማጠናቀቂያ በአጠቃላይ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ሙሉ ለሙሉ የፋይዳ መታወቂያ እንዲይዙ ይደረጋል ነው ያሉት። የሚሰጡ አገልግሎቶች ዲጂታል እንዲሆኑ መደረጉ ብልሹ አሰራርን ለማስቀረትና ፈጣን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑንም አንስተዋል።
ተሻሽሎ የቀረበው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ስትራቴጂ ለዘላቂ ልማት ጉልህ ፋይዳ አለው
Dec 25, 2025 34
አርባ ምንጭ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡- ተሻሽሎ የቀረበው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ስትራቴጂ ለዘላቂ ልማት ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ተገለጸ። በተሻሻለው የኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ሥልጠና ስትራቴጂ ላይ ያተኮረ ክልል አቀፍ የባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል። የደቡብበተሻሻለው የኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ሥልጠና ስትራቴጂ ላይ ያተኮረ ክልል አቀፍ የባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል። ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አማካሪና የጽሕፈት ቤት ኃላፊ ማሄ ቦዳ እንዳሉት፤ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ዘመኑን የዋጀ የሥራና የቴክኖሎጂ መፍጠሪያ የማድረግ ተግባር እየተከናወነ ነው። ተሻሽሎ የቀረበው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ስትራቴጂ ለዘላቂ ልማት ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመው፤ ኮሌጆች በክኅሎት የዳበረ ትውልድ ለመፍጠር የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። በየአካባቢው ያሉ ፀጋዎችን በመለየት ገበያው የሚፈልገውን ሥልጠና እንዲሰጡ የሚያበረታታ መሆኑን እና ይህም በመፍጠርና በመፍጠን እሳቤ በመሥራት ስኬት ለማምጣት እንደሚያስችልም አመላክተዋል። ስትራቴጂው የሰው ኃይል ዕድገትን ከኢኮኖሚ ለውጥ ጋር ለማስተሳሰር ያግዛል ያሉት ደግሞ የክልሉ ሥራና ክኅሎት ቢሮ ምክትልና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዘርፍ ኃላፊ በዛብህ ገበየሁ ናቸው። በተጨማሪም በትብብር የሚገነባ፣ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ የሚያጠናክር የልኅቀት ማዕከላትን ጥራትና ብቃት ብሎም የሰው ኃይል ተወዳዳሪነት የሚያረጋግጥ መሆኑን አስረድተዋል። የወጣቶችን ተስፋ የሚያድስ፣ ሥራ ፈጠራን የሚያበረታታ፣ የሙያ ሥነ-ምግባርን የሚያጎለብት በመሆኑ ከክልሉ የልማት ፀጋዎች ጋር ተጣጥሞ እንደሚሠራም አመላክተዋል። የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የቴክኖሎጂ መፍለቂያ፣ የማምረቻና የኢንዱስትሪ ሥፍራ በማድረግ የክልሉን ዕድገት ለማፋጠን በቅንጅት እንደሚሠራም ጠቁመዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በአገልግሎት አሰጣጥና በዜጎች አኗኗር ላይ መሰረታዊ ለውጥ አምጥቷል
Dec 25, 2025 60
አርባምንጭ ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡-የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትግበራ በአገልግሎት አሰጣጥና በዜጎች አኗኗር ላይ መሰረታዊ ለውጥ ያመጣ መሆኑን በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትግበራ በስኬት መጠናቀቁንና የ2030 ትግበራ በይፋ መጀመርን ማብሰራቸው ይታወቃል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትግበራ ትልቅ ስኬት የተመዘገበ መሆኑን በማንሳት በቀጣይ ደግሞ ተደራሽነትን የማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል የመፍጠር እና በዜጎችና በተቋማት መካከል ይበልጥ መተማመንን የማጎልበት ጉዳይ ትኩረት የሚደረግበት መሆኑን አስረድተዋል። በመሆኑም ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ የሃይል እና የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማስፋት ለተግባራዊነቱ መትጋት ይገባል ብለዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁራን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትግበራ በአገልግሎት አሰጣጥና በዜጎች አኗኗር ላይ መሰረታዊ ለውጥ ያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒቲንግና ሶፍትዌር ምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህርና የኤሌክትሮኒክ ትምህርት አስተዳደር ክፍል ዳይሬክተር መሐመድ አበበ (ዶ/ር)፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስኬት በዜጎች አኗኗር ላይ በተግባር የተገለጠ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገሪቱን ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ ካሻገሩ አንኳር ተግባራት መካከል አንዱ የግብይት ስርአቱ ዲጂታላይዝድ መሆን እንደሆነ አንስተው የመንግስት ግዥም በአብዛኛው ዲጂታል መሆኑ ብዙ ውስብስብ ችግሮችን ስለመፍታቱ አብራርተዋል። መንግስት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችን ለመቆጣጠር ብሎም አገልግሎትን ለማሳለጥ የዘረጋው የፋይዳ መታወቂያ ስርአትም ዜጎችን በብዙ መልክ ተጠቃሚ አድርጓል ብለዋል። በድመሩ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የሚታይ ለውጥና የሚቆጠር ውጤት የተገኘበት መሆኑን ገልጸው የ2030 ስትራቴጂን በላቀ ስኬት ለመከወን የሁላችንም እገዛ ያስፈልጋል ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የመረጃ ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር መምህር ኢያሱ ዲላ (ዶ/ር)፤ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬት መንግስት ቁርጠኛ አቋም ይዞ በመስራቱ የሚፈለገው ውጤት መጥቷል ብለዋል። በቴክኖሎጂ ታግዞ የተጀመረው መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ማግኘት ያስቻለ ዘመናዊ አሰራር መሆኑን አንስተው የኮደርስ ስልጠና፣ የባንክ አገልግሎቶች፣ የግብር ክፍያና ሌሎችም መንግስታዊ አገልግሎቶች የ2025 ስትራቴጂ ስኬት ማሳያዎች ናቸው ብለዋል። ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ከቀናት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ መደረጉ ይታወቃል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የሀገርን ሁለንተናዊ ልማትና እድገትን ለማሳካት ጠንካራ መሰረት አኑሯል
Dec 25, 2025 59
መቀሌ፤ታህሳስ 16/2018(ኢዜአ)፦የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የሀገርን ሁለንተናዊ ልማትና እድገት ለማሳካት ጠንካራ መሰረት ያኖረ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማጠናቂቂያ እና በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የማስመጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ መቶ በመቶ በሚባል ደረጃ የተሳካ መሆኑን ገልጸዋል። በስትራቴጂው በግብርና፣ በማዕድን ብሎም በኢንዱስትሪው እንደተገኘው ስኬት በዲጂታሉ ዘርፍም መገኘቱን አንስተው፥ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስኬት ፅኑ መሰረት እንደሚሆነው አመላክተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በትግራይ ክልል የሚሰሩ የዘርፉ ባለሙያዎች የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የሀገርን ሁለንተናዊ ልማትና እድገትን ለማሳካት ጠንካራ መሰረት ያኖረ መሆኑን ገልጸዋል። የሽግግር ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ባለሙያና ተመራማሪ የሆኑት ኢንጂነር ፍሰሃ ነጋ፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ አተገባበርና የተገኘው ስኬት አስደናቂ መሆኑን አንስተዋል። ከዚህም በመነሳት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ተግባራዊ ማድረግና ማሳካት የሚቻል መሆኑን ገልጸው፥ የዲጅታል አገልግሎትን ማስፋት ሀገራዊ ጥቅሙ ዘርፈ ብዙ ስለመሆኑ አስረድተዋል። በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የአይ ሲ ቲ ባለሙያዋ ወጣት ራሄል ገብረ ፃድቅ በበኩሏ፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የዜጎችን የአኗኗር ሁኔታ በፍጥነት የቀየረና ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን ገልፃለች። የዲጂታል አገልግሎት ከአገልግሎት ጥራትና ፍጥነትም ባለፈ የተገልጋዮችን እንግልት የሚያስቀርና የሀገርን ሃብት ከምዝበራ ለመታደግ የሚያስችል መሆኑን አንስታለች። በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የልማት ይዘቶች ባለሙያ ዳንኤል ገብረመስቀል፤ የመሬትን ጨምሮ የሃገር ሃብትን ለመቆጣጠርና ሌብነትን ለመከላከል የዲጂታል አሰራር ስርዓት የማይተካ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የዲጂታላይዜሽን አገልግሎት የአሰራር ፍጥነትን፣ ቁጥጥርንና ተጠያቂነትን ጭምር እውን በማድረግ ለዜጎች ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ብለዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ቁልፍ ትልሞች ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት መሆኑም ይታወቃል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ስፖርት
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ምድረገነት ሽሬን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሶስተኛ ከፍ አደረገ
Dec 25, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ11ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ምድረገነት ሽሬን 1 ለ 0 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ሀብታሙ በ95ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት ተጠባቂ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ የአፍሪካ ዋንጫ እና ሽልማቱ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ20 ነጥብ ደረጃውን ከአራተኛ ወደ ሶስተኛ ከፍ አድርጓል። በአንጻሩ በሊጉ ሶስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ምድረገነት ሽሬ በ14 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
የአፍሪካ ዋንጫ እና ሽልማቱ
Dec 25, 2025 98
የአፍሪካ ዋንጫ ሽልማት ለአህጉሪቷ እግር ኳስ ልማት ያለው መልካም አንድምታ፡- የአፍሪካ ዋንጫ የአህጉሪቷ ግዙፍ የስፖርት መድረክ ነው። የአፍሪካ ዋንጫ በተሳታፊ ሀገራት ብዛት፣ በፉክክር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው እይታ እያደገ ይገኛል። ይህም ውድድሩን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተመልካቾች እንዲያዩት እና ውድድሩን ስፖንሰር የማድረግ ፍላጎት እንዲያድግ ምክንያት ሆኗል። 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል። በውድድሩ 24 ሀገራት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለውድድሩ ተሳታፊ ሀገራት በርካታ ገንዘብ ለመሸለም ተዘጋጅቷል። ዋንጫ የሚያነሳው ሀገር የ10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ያገኛል። የአሸናፊ ሽልማት እ.አ.አ በኮትዲቭዋር ከተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሰባት ሚሊዮን ዶላር ሽልማት የ43 በመቶ ብልጫ አለው። ሁለተኛ የሚወጣው አገር የ4 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይበረከትለታል። በግማሽ ፍጻሜው የወደቁ ሁለት አገራት እያንዳንዳቸው 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር፤ በሩብ ፍጻሜው የተሰናበቱ አራት አገራት እያንዳንዳቸው 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ። በጥሎ ማለፉ ለሚሰናበቱ ስምንት ሀገራት እያንዳንዳቸው የ800 ሺህ ዶላር ሽልማት ይሰጣቸዋል። በምድባቸው ምርጥ ሶስተኛ ሆነው የሚያጠናቅቁ ሁለት ሀገራት በተመሳሳይ 700 ሺህ፣ በየምድባቸው አራተኛ ደረጃን ይዘው የሚያጠናቅቁ ስድስት ሀገራት እያንዳንዳቸው የ500 ሺህ ዶላር ሽልማት ይበረከትላቸዋል። 24ቱም ተሳታፊ ሀገራት በውድድሩ ላይ እንደሚያስመዘግቡት ውጤት የሽልማቱ ተቋዳሽ ይሆናሉ። የአፍሪካ ዋንጫን የሚያሸንፈው ሀገር በአጠቃላይ 11 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ሊያገኝ ይችላል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ዘንድሮ ያዘጋጀው ሽልማት እ.አ.አ በ2021 በካሜሮን አስተናጋጅነት ከተካሄደው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ጋር ሲነጻጸር የ40 በመቶ ብልጫ አለው። የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ (ዶ/ር) በአፍሪካ ዋንጫ እና በሌሎች የአፍሪካ ውድድሮች ላይ የታየው የሽልማት መጠን ማደግ በአህጉሪቷ እግር ኳስ የፋይናንስ እድገት የሚያሳይ እና የአፍሪካን የእግር ኳስ ምህዳር እንደሚደግፍ አመልክተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ እግር ኳስ ልማት፣ የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖች እና የእግር ኳስ ባለድርሻ አካላትን የሚደግፍ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ዋንጫ ሽልማት በአህጉራት ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች ላይ በሽልማት መጠኑ በሶስተኛ ደረጃ ላይ ይቀመጣል። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (ዪኤፋ) ለአውሮፓ ዋንጫ የ360 ሚሊዮን ዶላር አጠቃላይ ሽልማት የሚያዘጋጅ ሲሆን አሸናፊው ሀገር 30 ሚሊዮን ዶላር ያገኛል። ኮፓ አሜሪካ (ደቡብ አሜሪካ) አጠቃላይ ሽልማት 72 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ነው። አሸናፊው ሀገር 16 ሚሊዮን ዶላር ይወስዳል። የአፍሪካ ዋንጫ ሽልማት ከእስያ ዋንጫ እና የሰሜንና መካከለኛው አሜሪካ (ኮንካካፍ) ይበልጣል። እስያ ዋንጫ አጠቃላይ ሽልማቱ 15 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን ውድድሩን የሚያሸንፈው ሀገር አምስት ሚሊዮን ዶላር ያገኛል። ኮንካካፍ አጠቃላይ ሽልማት 15 ሚሊዮን የአሜሪካን ሚሊዮን ዶላር ነው። ዋንጫውን የሚያነሳው ሀገር የአምስት ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይበረከትለታል። የአፍሪካ ዋንጫ የገንዘብ ሽልማት እድገት ከአህጉሪቷ አልፎ ዓለም አቀፍ ትኩረትን የሳበ ጉዳይ ሆኗል። የገንዘብ ሽልማቱ ከጥቅም ባለፈ ለሀገራት የኢኮኖሚ ጠቃሜታዎችን የሚያስገኝ ነው። ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣው የአፍሪካ ዋንጫ ሽልማት ለአፍሪካ እግር ኳስ ልማት ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ማዕቀፍ ነው።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት ተጠባቂ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ
Dec 25, 2025 76
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይከናወናሉ። በአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 7 ሰዓት ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከምድረገነት ሽሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው 10 ጨዋታዎች በአራቱ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። ቡድኑ በ17 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ምድረገነት ሽሬ ከ10 የሊጉ ጨዋታዎች መካከል ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። አምስት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥቷል። ምድረገነት ሽሬ በ14 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሁለቱም ክለቦች በሊጉ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሊጉ ባደረጋቸው 10 ጨዋታዎች አምስቱን ሲያሸንፍ በአራቱ ተሸንፏል። በቀሪው አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይቷል። ቡድኑ በ16 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሊጉ እስከ አሁን ማሸነፍ የቻላቸው ጨዋታዎች ብዛት ሁለት ብቻ ናቸው። ሶስት ጊዜ ሲሸነፍ በአምስት ጨዋታዎች አቻ ወጥቷል። የ2016 ዓ.ም የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ11 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይጫወታሉ። ሸገር ከተማ ከሃዋሳ ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በሊጉ ባካሄዳቸው 10 ጨዋታዎች ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ አራት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ ሶስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። ቡድኑ በ12 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። በውድድር ዓመቱ ካከናወናቸው 10 ጨዋታዎች መካከል አምስቱን ያሸነፈው ሃዋሳ ከተማ ሶስት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። ሁለት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። ሃዋሳ ከተማ በ17 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። በሌላኛው መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ከድሬዳዋ ከተማ ከቀኑ 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኢትዮጵያ ቡና በ12 ነጥብ 14ኛ፣ ድሬዳዋ ከተማ በ13 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዘዋል። ጨዋታዎቹ በዋንጫ ፉክክሩ ግምት የሚሰጣቸው ናቸው።
ኮትዲቯር የአፍሪካ ዋንጫ ክብሯን የማስጠበቅ ጉዞ በድል ጀምራለች
Dec 25, 2025 66
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ስድስት የመጀመሪያ ጨዋታ ኮትዲቯር ሞዛምቢክን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በማራካሽ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የማንችስተር ዩናይትዱ የክንፍ ተጫዋች አማድ ዲያሎ በ49ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። የአማካይ ተጫዋቹ ፍራንክ ኬሲ ለዲያሎ ኳሱን አመቻችቶ አቀብሏል። በጨዋታው ላይ ኮትዲቯር በኳስ ቁጥጥር እና የግብ እድል በመፍጠር በተጋጣሚዋ ላይ ብልጫ ወስዳለች። የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ኮትዲቯር የዋንጫ ክብሯን የማስጠበቅ ጉዞ በድል ጀምራለች። ሞዛምቢክ ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃን ይዛለች። በዚሁ ምድብ ካሜሮን ከጋቦን ምሽት አምስት ላይ በአጋዲር ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ አርሶ አደሮች ምርታማነታቸው እንዲያድግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Dec 24, 2025 107
ባሕርዳር ፤ ታህሳስ 15/2018 (ኢዜአ)፡ - ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የተጎዳው መሬታቸው አገግሞ ምርታማነታቸው እንዲያድግ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው በባሕርዳር አስተዳደር የዘንዘልማ ቀበሌ አርሶ አደሮች ተናገሩ። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ዛሬ በዘንዘልማ ቀበሌ በንቅናቄ አስጀምሯል። በማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል። ከተሳታፊ አርሶ አደሮች ውስጥ የዘንዘልማ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ሙላት መኮንን ፤ ለዓመታት ያከናወንነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የልፋታችንን ዋጋ መልሶ እየከፈለን ነው ሲሉ ለኢዜአ ገልጸዋል። በዚህም ሰብልን ማብቀል ወደ ማቆም ተቃርቦ የነበረው መሬታቸው ለምነቱ እንዲጨምር በማድረጉ የሰብል ምርታማነታቸው እንዲያድግ ብሎም በቂ የእንስሳት መኖ እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው ተናግረዋል። በተጨማሪም በማሳቸው አካባቢ የተከሏቸው የማንጎና ሌሎች የፍራፍሬ ተክሎች ለውጤት በቅተው ተጠቃሚ እንደሆኑ አንስተው፤ዛሬ በተጀመረው ስራ ያለምንም ቀስቃሽ በንቃት መሳተፋቸውንና እንደሚቀጥሉበትም ገልጸዋል። አርሶ አደር ደስታው ማንዴ በበኩላቸው፤ ተጠቃሚነታችንን እያረጋገጠልን ያለው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ በመጀመሩ ተደስቼያለሁ ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወነው ስራ ምርታማነታቸው ማደጉን ገልጸው፤ ያገኘሁትን ጥቅም ለማሳደግም ዛሬ በተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ያለማንም ቀስቃሽ ወጥተን እየሰራን ነው ሲሉ ገልጸዋል። በባሕር ዳር ከተማ ዛሬ በተጀመረው የተፋሰስ ልማት ስራ በጥራትና በውጤታማነት ተምሳሌት እንዲሆን አስፈላጊው እገዛ እንደሚደረግ የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ መሰሉ ብርሃኑ ናቸው። ባለፉት ዓመታት የተራቆቱ አካባቢዎችን በመለየት የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ በመሰራቱና ከእንስሳት ንክኪ ነጻ በመደረጉ የአየር ንብረቱ እንዲስተካከልና የዝናብ መጠኑ እየጨመረ እንዲመጣ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። በሚለሙ ተፋሰሶች ላይ አርሶ አደሩ የፍራፍሬና የመኖ ችግኞችን እንዲተክል በማድረግ ዘላቂ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱን እንዲያረጋግጥ የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ፤ የዘንድሮው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ስራ በአስተዳደሩ ስር በሚገኙ በ12 የገጠር ቀበሌዎች በጥራት እንደሚካሄድ ገልጸዋል። በተለዩ ተፋሰሶች ከ1ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለማከናወን ዛሬ የተጀመረው ተግባር በቀጣይ ለ30 ቀናት እንደሚቆይ ተናግረዋል።
በመገጭ ግድብ አዋሳኝ በሆኑ ተፋሰሶች የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ማከናወን ተጀመረ
Dec 24, 2025 150
ጎንደር፣ ታኅሣስ 15/2018 (ኢዜአ)፡- የመገጭ የመስኖና የመጠጥ ውኃ ግድብን ከደለል ለመጠበቅ የሚያስችል ሕብረተሰቡን ያሳተፈ የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ዛሬ ተጀምሯል። የዘንድሮው የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት በጎንደር ከተማ አሥተዳደር ድባ ደፈጫ ቀበሌ ተካሂዷል፡፡ በዚሁ ወቅት የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው እንዳሉት፤ የዘንድሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ የመገጭ ግድብ አዋሳኝ በሆኑ 18 ተፋሰሶች ላይ ይካሄዳል። በዚህም መሠረት የማሳ እርከንና ክትር ሥራ እንደሚሠራና ሀገር በቀል ችግኞችም እንደሚተከሉ ጠቁመዋል። የጎንደር ከተማን ሕዝብ የረጅም ዓመታት የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ጥያቄ በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ እየተገነባ ያለውን ግድብ በደለል እንዳይሞላ ከወዲሁ መጠበቅ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ አርሶ አደሮች ምርታማነታቸው እንዲያድግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል በክልሉ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ ለማጠናከር ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል በዞኑ በአንድ ሺህ 52 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው በአሥተዳደሩ ሥር በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች 847 ሔክታር የሚሸፍን የእርከንና ክትር ሥራ በግድቡ ተፋሰሶች ይከናወናል ያሉት ደግሞ የከተማ አሥተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አበራ አደባ ናቸው፡፡ ለአንድ ወር በሚቆየው የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ከ8 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል። ቀደም ሲል በሕብረተሰቡ ተሳትፎ የተከናወኑ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራዎች የአፈር ለምነትን በመጨመር የሰብል ምርታማነት እንዲያድግ ማስቻላቸውንም አንስተዋል። በለሙ ተፋሰሶች በእንስሳት ማድለብ፣ በንብ ማነብ፣ በወተት ሀብትና በፍራፍሬ ልማት ዘርፍ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እየጨመረ መምጣቱንም አመላክተዋል። በሥራው የተሳተፉ አርሶ አደሮች በበኩላቸው፤ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ በአነስተኛ መሬት ብዙ ምርት እንድናገኝና ለእንስሳት በቂ የመኖ እንድናቀርብ አስችሎናል ብለዋል፡፡ የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ምንጮች ጎልብተው መስኖ እንዲጠቀሙ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸውም ጠቅሰዋል።
በክልሉ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ ለማጠናከር ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል
Dec 24, 2025 90
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁሉም ሰው የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተመላከተ። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ በዘንዘልማ ቀበሌ ዛሬ ተጀምሯል። በመርሃ ግብሩ የተገኙት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ መሰሉ ብርሃኑ እንዳሉት፤ የተጎዳ አካባቢን ወደ ነበረበት ለመመለስ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ማጠናከር ያስፈልጋል። ከተያዘው ወር መግቢያ ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በተለዩ ተፋሰሶች የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ዘንዘልማ ቀበሌ የተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ጣናን ከደለል የሚታደግ እንደሆነም ገልጸዋል። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የተጀመረው የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁሉም ሰው የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባም አመልክተዋል። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ ከዛሬ ጀምሮ ለ30 ቀናት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራው በ12 ቀበሌዎች በተለዩ 24 ተፋሰሶች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራው ጥራቱን በጠበቀና ዘላቂነት ባለው መልኩ በማከናወን ወደ ጣና ኃይቅ የሚገባውን ደለል መከላከል በሚያስችል አግባብ እንዲከናወን ክትትል እንደሚደረግ ተናግረዋል። በዘንዘልማ ቀበሌ በተጀመረው የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ መርሃ ግብር የክልልና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎችና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።
በዞኑ በአንድ ሺህ 52 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው
Dec 23, 2025 114
ደብረ ማርቆስ፤ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን በተያዘው የበጋ ወራት በአንድ ሺህ 52 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ።። በምስራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ባለሙያ አቶ ጤናው አላምረው ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአፈር እና የውሃ ጥበቃ ስራ የአፈር ለምነትን ጠብቆ በማቆየት ለሰብል ምርታማነት ማደግ የጎላ ሚና እያበረከተ ነው። እንዲሁም በተለያየ ምክንያት ተመናምኖ የቆየውን የደን ሃብት መልሶ በመተካት የደን ሽፋኑ ከፍ እንዲል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ይህንኑ ተግባር አጠናክሮ ለማስቀጠልም በዚህ የበጋ ወራት በ1 ሺህ 52 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልፀዋል። በተፋሰሶቹ ከ83 ሺህ 700 ሄክታር በላይ ለምነቱን ያጣ መሬት የሚሸፍን የልማት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራው ከታህሳስ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ሲሆን ለዚሁ የሚሆን የስራ መሳሪያ እና 39 ሺህ ቀያሽ አርሶ አደሮችን በማሰልጠን እንዲሳተፉ እየተደረገ ይገኛል። እስካሁን ስራ በተጀመረባቸው አካባቢዎችም ከአንድ ሺህ 800 ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ ማከናወን ተችሏል ነው ያሉት። የጥራት ደረጃውን ለማስጠበቅና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥም በየደረጃው የሚገኙ የግብርና ባለሙያዎች ለአርሶ አደሮች ሙያዊ እገዛና ድጋፍ እያደረጉ እንደሆነ አስረድተዋል። በአዋበል ወረዳ የጎደና ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ይመኑ መንግስቱ እንዳሉት፤ ቀደም ሲል በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የተከናወነበት ማሳ ለምነቱ በመሻሻሉ በሰብል ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ውጤት አስገኝቷል። ባገኙት ውጤት በመበረታታትም በዚህ የበጋ ወቅት በልማት ቡድን በመደራጀት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራውን እያከናወኑ እንደሚገኝም ገልፀዋል። በዞኑ ባለፈው ዓመት 56 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራ እንደተከናወነ ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቀን ነው - የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Dec 24, 2025 166
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ሲል የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ገለጸ። የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በኤርትራ መንግሥት አገዛዝ ደረሰብን ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ጋምቢያ(ባንጁል) የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ላቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን አድንቋል። በኤርትራ መንግስት ላይ የቀረቡትን ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክስ ተቀብሎ በመዝገብ ቁጥር 868/25 መመዝገቡን፣ የክሱ ፍሬ ነገር እና ይዘት ተቀባይነት ያለው መሆኑን እውቅና በመስጠት የኤርትራ መንግስት እንዲመልስ ክሱን መላኩን ኮሚሽኑ ማስታወቁን ገልጿል። የድርጅቱ ሊቀ-መንበር ኢብራሂም ሀሩን በመግለጫቸው እንደተናገሩት፤ የኤርትራው መንግሥት በደናክል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ህዝቦች እየፈፀመ ያለው መጠነ ሰፊ፣ ስልታዊ፣ መንግስታዊ መር እና ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በአሁኑ ወቅት እየደረሱ ነው ካሏቸው የመብት ጥሰቶች መካከልም ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ማካሄድ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት፣ በሺዎች የሚቆጠሩትን መሰወር፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ማከናወን መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰው፤ በተለይም ከ300ሺህ በላይ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማፈናቀል እና ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል፣ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋትና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን መጣስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ድርጅቱ የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ከ1993 ጀምሮ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰባቸው ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ክስ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እኤአ ጁን 04 ቀን 2025 በ122 ገጽ የተደራጀ ክስ ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የኤርትራ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን እንደገለጸላቸው ጠቁመዋል። ለክሱም ከተጠቀሙት ማስረጃዎች መካከል በድርጅቱ የተከናወነ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ግኝት፣ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝባዊ መብቶች በኤርትራ ላይ የተደረጉ ምርመራዎች፣ ግኝቶችና ማስረጃዎች፣ የመብት ጥሰት የደረሰባቸው የቀይ ባሕር አፋር ተጎጂ ወገኖች እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የተገኙ የሰብዓዊ መብት ምርመራዎችን መቅረቡን ተናግረዋል። ድርጅቱ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት መከራ ለማዳን፣ የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ድምፅ እንዲሆኑት፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡንና የኢሳያስ መንግስት ላይ ህጋዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጸንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው-ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
Dec 23, 2025 143
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እና ለረጅም ጊዜ ፀንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ኃላፊ አምባሳደር ኮንስታንሲያ አዴሊና ጋስፓራስ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቅርበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት (ዋይት ሃውስ) በተካሄደ ስነ ስርዓት የአምባሳደር ኮንስታንሲያን ሹመት በይፋ ተቀብለዋል። አምባሳደሯ በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ቢሮ ስራቸውን በይፋ ጀምረዋል። ዶናልድ ትራምፕ የአምባሳደር ኮንስታንሲያ የልዑኩ መሪ ሆኖ መመረጥ በጋራ የኢኮኖሚ እድሎች፣ በሉዓላዊ አመራር ሰጪነት እንዲሁም በሰላም እና ደህንነት ላይ የተመሰረተውን የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጽኑ አጋርነት የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በአፍሪካ ሰላም፣ ብልጽግና እና መረጋጋትን ማረጋገጥን ዋና ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የአጋርነት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኝ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት የማጠናከር ፍላጎት አላት -ተሰናባቹ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና
Dec 20, 2025 212
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ሽብርተኝነትን መዋጋትን ጨምሮ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት ለማጎልበት በጋራ መስራቷን እንደምትቀጥል ተሰናባቹ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና ገለጹ። አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ ትብብር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ያለው መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ሀገራቱ የኬንያው የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና መስራች አባት ጆሞ ኬንያታ እና ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ጊዜ አንስቶ ወዳጅነት እንደነበራቸው አውስተው ትብብሩ በከፍተኛ ደረጃ በሚደረጉ ጉብኝቶች እና ውይይቶች እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ጠንካራ አጋርነት ፈጥረው እየሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ጨምሮ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመዋጋት እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ሰላም እና ደህንነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ እና የኬንያ የንግድ ትብብር እያደገ መምጣቱን የገለጹት ተሰናባቹ አምባሳደር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብሩን አድማስ የበለጠ እንደሚያሰፋው ነው የተናገሩት። ቱሪዝም እና ንግድ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ ትስስር እንዲጎለብት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ፣ ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው የ"ላፕሴት ፕሮጀክት" እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ጨምሮ በሌሎች መሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ትስስሩን የሚያሳልጡ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባሳደር ጆርጅ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በማስመረቋ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ግድቡ በቀጣናው ሽግግርን የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1963 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ቀጣናዊ መረጋጋት እና ደህንነት ፣ ንግድ እና የመሰረት ልማት ትስስር የሀገራቱ ዋንጫ የትብብር መስኮች ናቸው።
ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ስለ ህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት ምን አሉ?
Dec 17, 2025 418
የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። በአድዋ ድል መታሰቢያም የአበባ ጉንጉን አኑረዋል። ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ስለ ህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት በስፋት ዘግበውታል። ዓለም አቀፍ የዜና ወኪሎቹ ሮይተርስ እና አሶሲዬትድ ፕሬስ ጉብኝቱን ከ"ጂኦ-ፖለቲካዊ" አንጻር ተመልክተውታል። በተለይ ህንድ በኢትዮጵያ ያላትን የአምስት ቢሊዮን ኢንቨስትመንት አጉልተዋል። አልጀዚራ ትኩረቱን ያደረገው ህንድ በ"ደቡባዊው ዓለም" (Global South) ላይ ያላትን ተጽዕኖ ለማሳደግ በምታደርገው ጥረት ላይ ነው። እንዲሁም የኢትዮጵያና የህንድ ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመካከለኛው ምስራቅና በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ፋይዳም በስፋት አንስቷል። ቢቢሲ እና ፍራንስ 24 ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለየት ያለ አቀባበል ትልቅ የዲፕሎማሲያዊ መቀራረብ ምልክት መሆኑን ዘግበውታል። የአፍሪካ ሚዲያዎች በበኩላቸው የናሬንድራ ሞዲን ጉብኝት "የአፍሪካ-ህንድ" ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ አድርገው ዘግበዋል። አፍሪካ ኒውስ እና ዘ ኢስት አፍሪካን ጉብኝቱ በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መደረጉን በማንሳት፣ ህንድ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ወታደራዊ፣ የጤና እና የቴክኖሎጂ ትብብር እንደሚያጠናክረውም ገልጸዋል። የደቡብ አፍሪካው ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ የናይጄሪያ እና ሌሎች የአፍሪካ መገናኛ ብዙሃን ህንድ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ኢትዮጵያን እንደ መግቢያ በር (Anchor) መጠቀሟን እና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የሚኖረውን ተምሳሌትነት ዘግበዋል። እንደ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ (The Times of India) ፣ ኤንዲቲቪ (NDTV) እና ኤኤንአይ (ANI) ያሉ የህንድ መገናኛ ብዙሃን የሞዲን ጉብኝት ከፍተኛ ሽፋን ሰጥተውታል። የዘገባዎቹ ዋንኛ ትኩረት በኢትዮጵያ ፓርላማ ስላደረጉት ንግግር እና ስለተደረገላቸው ልዩ የክብር ሽልማት ነው። በሌላ በኩልም የዲጂታልና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተደረጉ ስምምነቶችን በዝርዝር አቅርበዋል። አጠቃላይ የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ትኩረት ታሪክ፣ ስትራቴጂካዊ አጋርነት፣ የደቡብ ለደቡብ ትብብር ላይ ያጠነጠኑ ናቸው። የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ መሸጋገሩንም በመገናኛ ብዙሃኑ በስፋት ተነስቷል። ኢትዮጵያ እና ህንድ የተባበሩት መንግስታ ድርጅት እና ብሪክስን ጨምሮ በሌሎች የባለብዙወገን መድረኮች ላይ የደቡባዊውን ዓለም ድምፅ ለማሰማት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸው በዘገባዎቹ በስፋት ተንጸባርቋል።
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 335
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 539
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 862
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል። የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 1060
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 693
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3124
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 3058
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3959
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 2558
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1644
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7459
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5946
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ እና የህንድ ዘመን አይሽሬ እና ድንበር ተሻጋሪ ወዳጅነት
Dec 16, 2025 453
በሙሴ መለስ (ኢዜአ) ኢትዮጵያ እና ህንድ ረጅም ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አላቸው። በዚህም የስልጣኔ እሴቶችን ይጋራሉ። ሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከፈጠሩ ከ2000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እና ህንድ ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳሽነት እንደሆነም ይወሳል። ኢትዮጵያ እና ህንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1948 ነው። እ.አ.አ በ1950 ሳርዳት ሳንት ሲንግ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያ እና ህንድ በየሀገራቱ ኤምባሲ በመክፈት የዲፕሎማሲ ትብብሩን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ገልጸዋል። ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ እ.አ.አ በ1956 እና በ1958 በህንድ ያደረጓቸው ጉብኝቶች ከኢትዮጵያ መሪዎች ጉብኝቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። እ.አ.አ 1960 ዎቹ ማብቂያ እና 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የህንድ ፕሬዝዳንቶች የነበሩት ሳርቬፓሊ ራድሃክሪሽናን እና ዛኪር ሁሴን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝቶችን አድርገዋል። እ.አ.አ በ2011 ከአንድ ዓመት በፊት ህይታቸው ያለፈው የቀድሞው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንሞሃን ሲንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝትም ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው የህንድ ፕሬዝዳንት ራም ናት ኮቪንድ እ.አ.አ በ2017 የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ በጉብኝታቸው ህንድ እና ኢትዮጵያ በንግድ፣ ኮሙኒኬሽን እና የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 15ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የሀገራቱ መሪዎች በወቅቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ የወጣቶች ክህሎት ማጎልበት እና በሕዝብ ለሕዝብ ልውውጥ ዙሪያ ትብብርን በማጠናከር ዙሪያ ተወያይተዋል። በወቅቱ ህንድ ባዘጋጀችው የሁለተኛው “Voice of Global South Summit” በተሰኘው ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተሳትፎ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲ በህንድ አጠቃላይ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈውም ነበር። የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን የደስታ መግለጫ መልዕክት በመቀበል በአዲሱ የስልጣን ዘመናቸው ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት አጋርነት እንደሚያድግ መግለጻቸውም ይታወሳል። ህንድ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላቸውን አጋርነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። በዚህም ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ትብብር ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥም ነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ያስታወቁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 20ኛው የቡድን 20 አባላት ሀገራት ጉባኤ ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ትርጉም ያለው እና ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ህንድ የቡድን 20 አባል ሀገር መሆኗ የሀገራቱን የባለብዙ ወገን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር ነው። ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ሀገራቱ የሁለትዮሽ እና የባለዙወገን ትብብራቸውን የሚያጠናክሩ ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በወቅቱ የህንድ የትምህርት፣ ንግድ፣ ልማት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የሀገራቱ ግንኙነት የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ድጋፍ ያደረገች ሲሆን በብዝሃ ወገን ማዕቀፉ ሁለቱ ሀገራት በትብብር እየሰሩም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ህንድ በተለያዩ ጊዜያት በአየር ትራንስፖርት፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ መከላከያ፣ ተደራራቢ ታክስን የማስቀረት፣ ንግድ፣ ኮሙኒኬሽን ሳይንስ፣ባህል፣ ትምህርት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መስራት የሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 2025 ኢትዮጵያ እና ህንድ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ የተፈራረሙት የሁለትዮሽ ስምምነት ቁልፍ የሚባል ነው። እ.አ.አ በ2023/24 በወጣ መረጃ የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ምጣኔ 271 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ኢትዮጵያ አተር፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቆዳ ውጤቶች እና የከበሩ ድንጋዮችን ወደ ህንድ ትልካለች። ከህንድ ደግሞ ማሽነሪዎች፣ የመድኃኒትት ምርቶች እና የብረታ ብረት ውጤቶችን በዋናነት ታስገባለች። ህንድ የኢትዮጵያ ዋንኛ የኢንቨስትመንት አጋር ከሚባሉ ሀገራት መካከል ትጠቀሳለች። ከ500 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በጨርቃ ጨርቅ፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ። ህንድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ታደርጋለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ጤና እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከሁለቱ ሀገራት አበይት የትብብር መስኮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ የጉብኝታቸው መርሃ ግብር ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶች እና የጉብኝት ልውውጦች የኢትዮጵያ እና የህንድን ግንኙነት የበለጠ የሚያጸኑ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ህንድ በታዳሽ ኃይል፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ግብርና ማቀነባበሪያን ጨምሮ በአዳዲስ መስኮች ትብብራቸውን የማጠናከር ጽኑ ፍላጎት አላቸው። የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከእርስ በእርስ ግንኙነት ባለፈ የአፍሪካ እና ህንድ እንዲሁም የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። ከ2000 ዓመት በፊት የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ጠንካራ እና ጽኑ ትብብር ተቀይሯል። በማይናወጥ መሰረት ላይም ቆሟል። የበለጠ ጥልቀቱ እየጨመረ የመጣው የሀገራቱ ግንኙነት በጋራ ብልጽግና፣ ስትራቴጂካዊ ትስስር፣ ዘላቂ ልማት እና የሀገራቱን ዜጎች ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ ቁርጠኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 963
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው። እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም። የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል። የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል። ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!