ቀጥታ፡

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሕዝባዊ ውይይቶች አጀንዳዎችን ያሰባሰበበት የእስካሁኑ የምክክር ሂደት ቁልፍ ባሕርያት

 

👉 ባለድርሻ አካላት እንደሀገር ያልተግባባንባቸውን እጅግ መሠረታዊ የሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች በውይይት በማዳበር ለኮሚሽኑ ማስረከባቸው፤

👉 የብዙ ባለድርሻ አካላት ሕመሞች፣ ሥጋቶች፣ ምኞቶች እና ተስፋዎች በአጀንዳ መልክ መቅረባቸው፤

👉 በሂደቱ ኮሚሽኑ ለምክክሩ ሂደት የሚጠቅሙ እጅግ በርካታ ግብዓቶችን መሰብሰቡ፤

👉 በአንፃራዊነት የተሳታፊዎችን ምቾት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለተሳታፊዎች ቅርብ ናቸው ተብለው በሚታሰቡ ቦታዎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት መከናወኑ፤

👉 በሕዝባዊ ውይይት አጀንዳን የመሰብሰብ ሥራ ሁለት ዓመታትን ፈጅቷል፤

👉 በአጠቃላይ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔው መካሄድ እንደ ቅድመ ሁኔታ በማገልገል የራሱን ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።

Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ምክክር

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም