ቀጥታ፡

የኳታር ኤሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል-ታኒ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-የኳታር ኤሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል-ታኒ  ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኳታሩ ኤሚር የብልጽግና ፓርቲ በጠቅላላ ምርጫው ያስመዘገበውን ድል ተከትሎ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንኳን ደስ አላችሁ የደስታ መግለጫ መልዕክት ልከዋል።

ኤሚሩ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ስኬትን የተመኙ ሲሆን፣በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ እንዲያድግና እንዲጠናከር ያላቸውን ፅኑ ፍላጎትም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም