ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የሐይማኖት አባቶች ለአብሮነት መጎልበት ከመቼውም ጊዜ በላይ የላቀ ሚናቸውን እንደሚወጡ ገለጹ
Dec 26, 2025 21
ባሕር ዳር፤ ታኅሣስ 17/2018 (ኢዜአ)፡- ለሀገር ሰላም፣ ፍቅርና አብሮነት መጎልበት የላቀ ሚናችንን መወጣታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የተለያዩ የሐይማኖት አባቶች ተናገሩ። ''ዘካሪ መካሪ የሐይማኖት አባት ለዘላቂ ሰላምና ልማት'' በሚል መሪ ሐሳብ ከሰሜን ጎጃም ዞን የተውጣጡ የተለያዩ የሐይማኖት አባቶች የተሳተፉበት መድረክ በባሕር ዳር ከተማ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት የመድረኩ ተሳታፊዎች ለሀገር ሰላምና ልማት መጎልበት የሀገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶች ሚና የላቀ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። የሰላም ግንባታ ሂደት ያለ ሐይማኖታዊና የሞራል ዕሴቶች ስኬታማ ስለማይሆን እነዚህን ለማስጠበቅ አጠቃላይ ምዕመኑንና ወጣቶችን ማስተማር ይገባል ብለዋል። በክልሉ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሐይማኖት አባቶች ሚናቸውን ይበልጥ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ቄስ ታዘበው ጌታሁን በሰጡት አስተያየት፤ የሰላም መታጣት በተለያዩ አካባቢዎች ሁላችንንም ዋጋ እያስከፈለን በመሆኑ ከምንም በላይ ለሰላም ዘብ መቆም ይገባናል ብለዋል። የሰላም ግንባታ ከግለሰብ ጀምሮ ወደ ቤተሰብና ሀገር የሚዘልቅ በመሆኑ እያንዳንዱ ግለሰብ ስለ ሰላም አደራና ኃላፊነት ያለበት መሆኑንም አስገንዝበዋል። ሼኽ ሙሐመድ አደም በበኩላቸው፤ የሰላም ጉዳይ የእያንዳንዳችን ጥረትና ትጋት ውጤት በመሆኑ ሁላችንንም ይመለከተናል ብለዋል። የጥፋት እንቅስቃሴን በማውገዝና ከጥፋት እንዲመለሱ በመምከር ጭምር የሰላም ዕሴቶች እንዲጎለብቱ በተለይም የሐይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የላቀ ሚናችንን መወጣት አለብን ሲሉ ተናግረዋል። የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አሰፋ ጥላሁን፤ የሐይማኖቶች ዕሴቶች ሰላምን፣ ፍቅርን፣ አንድነትን፣ ይቅርታንና መልካምነትን የሚሰብኩ በመሆኑ የአባቶች ትምህርት ትልቅ ትርጉም እንዳለው አንስተዋል። በመሆኑም የሐይማኖት አባቶች አጥፊዎችን መክሮ በመመለስ፣ በመልካም ተግባራት የተሰማሩትን በማመሥገን ለሰላም ዕሴቶች ግንባታ የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የሐይማኖት አባቶች የሰላም ጠባቂ፣ መካሪና አስታራቂ በመሆን የጀመሩትን ሥራ መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በክልሉ የተፈጠረውን ችግር በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት መንግሥት ብዙ መሥራቱን አስታውሰው በቀጣይም አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። በአንጻሩ የሰላም ጥሪ በመግፋት በጥፋት የሚቀጥሉ አካላት ላይ መንግሥት የተጠናከረ ርምጃ በመውሰድ ሕግ የሚያስከብር መሆኑንም ነው ያስታወቁት።
የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ የተዘጋጀ ነው
Dec 26, 2025 37
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ መዘጋጀቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፥ የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ረቂቅ ፖሊሲን አስመልክቶ ከዲጂታል ካውንስል አባላት ጋር በበይነ መረብ ውይይት አካሂደዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በሁሉም መስክ የሥራ ፈጠራ ባህልን በማስረጽ ቀጣይነት ያለው እና ፈጣን ዕድገትን ዕውን ለማድረግ ኢንተርፕረነርሽፕ ቁልፍ መሳሪያ ነው ብለዋል። ፖሊሲው በዋናነት ሁሉን አቀፍ እና አካታች ሀገራዊ የኢንተርፕረነርሽፕ ንቅናቄን በማቀጣጠል በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ የዲጂታል ሥራ ፈጠራንና ተወዳዳሪነትን የሚያበረታታና የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። የፖሊሲ ማዕቀፉ ችግር ፈች ማህበረሰብን ለመገንባት፣ የፈጠራ ባህልን ለማጎልበት፣ እሴትን ለመጨመር እንዲሁም ምቹ ስነምህዳርን ለመገንባት የሚያስችል የኢኮኖሚ ዕድገት ማዕቀፍ እንደሆነም ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያን የኢንተርፕረነርሽፕ ስነ-ምህዳርና የስራ ፈጠራ ውጥኖችን አቅጣጫ በመስጠት የመምራት ቁልፍ ሚና አለው ነው ያሉት። በተለይ የኢንተርፕረነርሽፕ ስነ-ምህዳሩን ሊያሻሽሉ የሚችሉ የጋራ አመለካከቶችን፣ እምነቶችንንና ባህሪያትን ለማጎልበት በእጅጉ እንደሚያግዝ አብራርተዋል። በውይይቱ የልማት ፖሊሲው የታለመለትን ውጤት ማምጣት እንዲችል በፖሊሲው ትግበራ ወቅት የሚታዩ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖችን በመለየት በየደረጃው ወጥና ጠንካራ የክትትል ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ከዲጂታል ካውንስሉ ጋር መግባባት መፈጠሩን ገልጸዋል። በኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ እና ግብዓቶችን በመጨመር የልማት ፖሊሲ ሰነዱ ወደ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ተልኮ እንዲፀድቅ መወሰኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድን ጋር አቻ ተለያየ
Dec 26, 2025 32
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት ሲዳማ ቡና እና ኢትዮጵያ መድን ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቋል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ረመዳን በ18ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ መድን መሪ ሆኗል። ብርሃኑ በቀለ በ29ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል ሲዳማ ቡናን አቻ አድርጋለች። የሲዳማ ቡናው አጥቂ ሀብታሙ ታደሰ ከእረፍት መልስ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። ውጤቱን ተከትሎ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ነጥቡን ወደ 22 ከፍ አድርጓል። ከተከታዩ ፋሲል ከነማ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ለማስፋት ያገኘውን እድል አልተጠቀመም። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ13 ነጥብ ደረጃውን ከ16ኛ ወደ 13ኛ ከፍ አድርጓል። ዛሬ በተደረገው ሌላኛው ጨዋታ መቻል አዳማ ከተማን 3 ለ 1 አሸንፏል። መቻል ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል ጨዋታዎቹን ተከትሎ የ11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የ12ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ እንደሚካሄዱ የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል።
መገናኛ ብዙሃን ብሔራዊ ትርክትን ለመገንባት ቅድሚያ ሰጥተው መስራት ይጠበቅባቸዋል
Dec 26, 2025 34
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦መገናኛ ብዙሃን የሀገር ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርና የብሔራዊነት ትርክትን ለመገንባት ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ ገለጹ። 48ኛው የ"ጉሚ በለል" የውይይት መድረክ "ብሔራዊ ጥቅም እና መገናኛ ብዙሃን" በሚል መሪ ሐሳብ በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ተካሂዷል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ በዚሁ ወቅት፤ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም በትውልድ የማይገደብ መሆኑን ገልጸዋል። መገናኛ ብዙሃንም ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው ገልጸው፤ የሕዝብ አንድነትን ለማጠናከር እንዲሁም የኢትዮጵያን ተደማጭነት ለማሳደግ ግንባር ቀደም ሚናቸውን መወጣት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። ለብሔራዊ ትርክት ግንባታ እና ሐሰተኛ መረጃን ለመከላከል በትኩረት መሥራት እንዳለባቸውም ተናግረዋል። የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ጥረት ግንባር ቀደም መሆን እንዳለባቸው ጠቁመው፤ ለአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮችም ትኩረት መስጠት ይገባቸዋል ብለዋል። የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ እንደገለጹት፤ መገናኛ ብዙሃን ብሔራዊ ጥቅም ከማስጠበቅ አኳያ የማይተካ ሚና አላቸው። ስለሆነም መገናኛ ብዙሃን ለሀገር እና ሕዝብ ጥቅም ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው ነው ያመለከቱት። መገናኛ ብዙሃን ለገጽታ ግንባታ ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ኃይሉ፤ በጎ ገጽታን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማስተዋወቅ ረገድ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆናቸውን አመልክተዋል። ለዚህ ስኬት ዘመኑን የዋጁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መታጠቅ እንዲሁም የሰለጠነ የሰው ሃይል ማሟላት እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየትም መገናኛ ብዙሃን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበርና ሉዓላዊነት መጠበቅ ሚናችንን እናጠናከራለን ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተፈራ በቀለ፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ የመገናኛ ብዙሃን ቀዳሚ ተግባር መሆን ይገባዋል ብለዋል፡፡ ከዚህም አኳያ ኢዜአ የሀገርን ገጽታ የሚገነቡ፣ ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ እንዲሁም ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎችን በግንባር ቀደምትነት እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቢንያም ኤሮ፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ ከምንም በፊት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ ተቋማቸው ብሔራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ የይዘት ስራዎችን በመሥራት የብሔራዊ ትርክትን ለመገንባት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አድማሱ ዳምጠው፤ መገናኛ ብዙሃን በተደመረ አቅም ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር በጋራ መትጋት አለባቸው ብለዋል፡፡ የኤን ቢሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዋና ስራ አስፈጻሚ ብሩክ ከበደ በበኩላቸው፤ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ከሀገር ብሔራዊ ጥቅም አኳያ ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ስልጠና እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። የኦቢኤን ዋና ዳይሬክተር አቶ ፍሰሃ በላይነህ ፤ መገናኛ ብዙሃን ማስገንዘብ፣ የማጋለጥ እና የመከላከል ሚናውን ማጠናከር አለበት ብለዋል፡፡ በኦሮሚያ ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት እና በኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ትብብር የሚዘጋጀው የ"ጉሚ በለል" መድረክ በተለያዩ ወቅታዊና ስትራቴጂካዊ ሀገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ምሁራንና የሥራ ኃላፊዎች የሚወያዩበት መድረክ ነው።
የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ
Dec 26, 2025 35
ባሕርዳር፤ ታሕሳስ 17/2018(ኢዜአ)፡ - የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ የተሻሻለውን የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን ጨምሮ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ። የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ በፌዴራል ደረጃ ተሻሽሎ ከፀደቀው ጋር እንዲጣጣም ተደርጎ የወጣ መሆኑም ተመላክቷል። የክልሉ መሬት ቢሮ ኃላፊ ሲሳይ ዳምጤ ለምክር ቤቱ እንደገለጹት፤ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል ነው። የገጠር መሬት ባለመብቶች መሬታቸውን ማከራየት፣ በዋስትና ማስያዝ፣ ከባለሃብቶች ጋር በጋራ ማልማትና በውርስ ወይም በስጦታ ለማስተላለፍ የሚፈቅድ እንደሆነ አስረድተዋል። አርሶ አደሩ የመሬት ይዞታ ዋስትና በመስጠት ያፈራውን ንብረት የመጠቀም መብትን ለማጠናከርና የገጠር መሬት ምዝገባ መረጃ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለማደራጀት የሚያስችል መሆኑንም አንስተዋል። እንዲሁም የሴቶችና ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን የመሬት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ አካታች የመሬት አጠቃቀም ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችልም አመልክተዋል። የምክር ቤቱ የግብርናና አካባቢ ጥበቃና ውሃ ሃብት ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከፍያለው ሙላቴ በበኩላቸው፤ የአዋጁ መፅደቅ ከመሬት ጋር ተያይዞ ይነሱ የነበሩ ችግሮችን በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ ጉባዔ በተጨማሪም የፕሮጀክት አስተዳደርና አመራር ስርዓት ፣ የኤክስሳይዝ ታክስን ለማሻሻል የወጣን አዋጅና የተሻሻለው የመንግስት ሰራተኞች አስተዳደርን ጨምሮ ሌሎች አዋጆች ላይ ተወያይቶ አፅድቋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ፖለቲካ
የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ
Dec 26, 2025 35
ባሕርዳር፤ ታሕሳስ 17/2018(ኢዜአ)፡ - የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ የተሻሻለውን የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን ጨምሮ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ። የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ በፌዴራል ደረጃ ተሻሽሎ ከፀደቀው ጋር እንዲጣጣም ተደርጎ የወጣ መሆኑም ተመላክቷል። የክልሉ መሬት ቢሮ ኃላፊ ሲሳይ ዳምጤ ለምክር ቤቱ እንደገለጹት፤ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል ነው። የገጠር መሬት ባለመብቶች መሬታቸውን ማከራየት፣ በዋስትና ማስያዝ፣ ከባለሃብቶች ጋር በጋራ ማልማትና በውርስ ወይም በስጦታ ለማስተላለፍ የሚፈቅድ እንደሆነ አስረድተዋል። አርሶ አደሩ የመሬት ይዞታ ዋስትና በመስጠት ያፈራውን ንብረት የመጠቀም መብትን ለማጠናከርና የገጠር መሬት ምዝገባ መረጃ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለማደራጀት የሚያስችል መሆኑንም አንስተዋል። እንዲሁም የሴቶችና ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን የመሬት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ አካታች የመሬት አጠቃቀም ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችልም አመልክተዋል። የምክር ቤቱ የግብርናና አካባቢ ጥበቃና ውሃ ሃብት ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከፍያለው ሙላቴ በበኩላቸው፤ የአዋጁ መፅደቅ ከመሬት ጋር ተያይዞ ይነሱ የነበሩ ችግሮችን በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ ጉባዔ በተጨማሪም የፕሮጀክት አስተዳደርና አመራር ስርዓት ፣ የኤክስሳይዝ ታክስን ለማሻሻል የወጣን አዋጅና የተሻሻለው የመንግስት ሰራተኞች አስተዳደርን ጨምሮ ሌሎች አዋጆች ላይ ተወያይቶ አፅድቋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ነው
Dec 25, 2025 180
ባሕርዳር ፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ) ፡- የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር፤ አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔ በባሕርዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፤ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በቅርቡ የተፈራረመው የዘላቂ ሰላም ስምምነት በክልሉ ሰላምን ለማፅናት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የክልሉ መንግስት ችግሮችን በውይይትና በንግግር መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲያቀርብ የነበረው የሰላም አማራጭ ፍሬ ማፍራቱን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል። ግጭት ይብቃ ብለው የክልሉን መንግስት የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለተመሰሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን ምክር ቤቱ ያመሰግናል ያሉት አፈ ጉባኤዋ ፤ ሌሎች በጫካ የቀሩ ታጣቂዎችም የሰላም ጥሪውን ተቀብለው እንዲመጡ ጠይቀዋል። የአማራ ክልል መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን ገልጸው ፤ አጠናክሮ እንዲቀጥል በምክር ቤቱ በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ትብብር የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክር ቤት አባላት ለመልካም አስተዳደር መስፈን፣ ለዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበርና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተያዘው ዓመት የሚካሄደው 7ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተአማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅና ህዝቡ በምርጫው በንቃት እንዲሳተፍ የምክር ቤት አባላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። ምክር ቤቱ የክልሉን ትምህርት ቢሮ የ5 ወራት እቅድ አፈፃፀምና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በተከናወኑ የፋይናንስ ህጋዊነትና ክዋኔ ኦዲት ግኝቶች ላይ እንደሚመክር ከመርሃ ግብሩ መረዳት ተችሏል። በጉባዔው ልዩ ልዩ አዋጆችና ሹመቶች እንደሚጸድቁም ይጠበቃል።
የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ ለውጦችን በሚያሳይ መልኩ ይከበራል
Dec 25, 2025 164
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ ከጥር 15 እስከ 19 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከበር በኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ ገለፁ። በበዓሉ ላይ "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በሚል የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብም ተመላክቷል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ፤ የአየር ኃይሉን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል መሪ ሃሳብ ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ደማቅ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር አስታውቀዋል። በበዓሉ ከጥር 15 ቀን ጀምሮ በሚካሄደውና "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በተሰኘው መርሃ ግብር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብ አመላክተዋል። በዚህም የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ የሩሲያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይሎች በጋራ በመሆን የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት እንደሚያቀርቡ ጠቅሰዋል። "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ የቻይና፣ ህንድ፣ አሜሪካ እና ደቡብ አፍሪካ ግዙፍ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ኤክስፖ እንደሚካሄድም ገልፀዋል። ከ25 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ የቴክኖሎጂ ተቋማት የደረሱበትን ደረጃ ለጉብኝት ክፍት የሚያደርጉበት "ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2026" እንደሚካሄድም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የአቪዬሽን ማዕከል መሆኗን የምታረጋግጥበት "ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም" ለሶስተኛ ጊዜ እንደሚካሄድም ተናግረዋል። "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው መድረክ ላይ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦችና ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች ይታደማሉ ነው ያሉት። የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አዛዦችና የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል ርዕስ ከህዝቡ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ጠቅሰዋል። በዓሉ የአየር ኃይሉን የ90 ዓመት የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በማሳየት ይከበራል ነው ያሉት። መላው የሀገሪቱ ህዝብ በዚህ ታሪካዊ በዓል ላይ በመገኘት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የደረሰበትን ዝግጁነት እንዲመለከት ጥሪ አቅርበዋል። የበዓሉ አካል የሆነና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ሃሳብ ባሳለፍነው ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ የ10 ኪሎ ሜትር ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ሩጫ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይህ ውድድር በህዝብና በተቋሙ መካከል ያለውን ትስስር ያጠናከረና ለዋናው በዓል መሰረት የጣለ ታሪካዊ ኹነት ሆኖ ማለፉንም ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
Dec 25, 2025 121
ባሕር ዳር፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔውን መካሄድ ጀምሯል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ የአምስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለጉባዔው ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል። በውይይቱ በትምህርት አጀማመርና በተከናወኑ ተግባራት ላይ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ተጠቁሟል። እንዲሁም በክልሉ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የፋይናንስ ሕጋዊነትና የክዋኔ ኦዲት ግኝቶችንና የተሰጡ የማሻሻያ ሐሳቦችን የሚያሳይ የተጠቃለለ ሪፖርት ላይ እንደሚመክር ተመላክቷል። ጉባዔው ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፤ በቆይታው ልዩ ልዩ ዐዋጆች እና ሹመቶችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።
መንግሥት ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል-የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Dec 24, 2025 208
አዲስ አበባ፣ታኅሣስ 15/2018(ኢዜአ)፡-መንግሥት የሀገር ግንባታ ሂደቱን ለማጽናት እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል፡፡ እነዚህ ሦስቱ ምሰሶዎች ሀገራዊ አንድነትን፣ሰላምና ብልጽግናን፣ እንዲሁም ዜጎች በመተማመን እና በተጠያቂነት ላይ የተመሠረተ የጋራ ራዕይ እንዲኖራቸዉ የሚያደርጉ ቁልፍ መሰረቶች ናቸው፡፡ ዲሞክራሲን የመገንባት ሂደት ለአንድ ሀገር ወሳኝ ተግባር ሲሆን፣ በዋናነት ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቁ ተቋማትን ማቋቋም ላይ ትኩረት ያደረገ ነዉ፡፡ተቋማቱ የሚመሩባቸዉ ህጎችና የአሰራር ሥርዓቶች፣የተቋማቱ አወቃቀርና አደረጃጀት፣ እንዲሁም ለህዝብ ያላቸዉን ተዓማኒነትን መጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራበት ይገኛል፡፡ ጠንካራ የዲሞክራሲ ባህልና ሥርዓት የሚገነባው ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት ሲፈጠሩና ሲጠናከሩ መሆኑን መንግሥት በጽኑ የሚገነዘበው ጉዳይ ነዉ፡፡በዚህም ኢትዮጵያ ባለፉት 7 ዓመታት በዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ሂደት ውስጥ ሁለተናዊ ሪፎርም ሥራዎችን ስታከናውን ቆይታለች፡፡ እነዚህ ሪፎርሞች የሀገሪቱን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑትን የዲሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እና ጠንካራ አድርጎ ለመገንባት መንግሥት ምን ያህል ቁርጠኛ እንደሆነ ያሳየባቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ተቋማት መጠናከር በአንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም እና ልማት እንዲረጋገጥ እንደ ዋንኛ ምሰሶ የሚወሰድ ነው፡፡ በተለይም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ የታዩ ተጨባጭ ለውጦች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ለመጠበቅ፣ እንዲሁም የሕዝቡን ዕምነት ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ መንግሥት በተለይ ተቋማዊ ዐቅምን በማሳደግ እና ነፃነትን በማረጋገጥ፣ የዲሞክራሲ ምህዳርን እንዲሰፋ ለማደረግ የሚጠበቅበት ግዴታ ብቻ ሳይሆን ዲሞክራሲ የሚያብብበትን አስቻይ ዐውድና ማዕቀፍ ለመፍጠር ዓለማው አድረጓል፡፡ ይሄንን ከግብ ለማድረስ በተለይ የፀጥታ፣ የፍትሕ፣ የሲቪልና የሚዲያ ተቋማት፣ እንዲሁም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕዝብን ማዕከል አድርገው እንዲሰሩ መንግሥት በቁርጠኝነት በመደገፉ እንደ ሀገር ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ በማደርረግ ተጨባጭ ዉጤቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል፡፡ ሌላው መንግስት በትኩረት እየሰራበት ያለው ጉዳይ እንደ ሀገር ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ነዉ፡፡ ይህ ሂደት ዋና ዓለማ ያደረገው መላዉ ሕዝብ፣ ተቋማት፣ አመራርና ሠራተኛዉ በሀገራዊ ራዕይ ላይ በተለያዩ ድምጾች የጋራ እድገትን በመገንባት ሀገራዊ ህለውና እና ብልጽግና እንዲረጋገጥ እንዲሁም በዜጎች መካከል መተማመን እና ሀገራዊ አንድነትን እንዲፈጠር ማድርግ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ የብዙሃን ድምጽ የሚሰማበት የፖለቲካ ዐዉድ ለመፍጠር አያሌ የፖለቲካ ማሻሻያዎችን አድርጋለች፡፡ በዚህም እስከዛሬ በነበሩ መንግሥታት ያለተሞከረውን ጫፍ ወጥተው የሚታዩ ተቃርኖ ሀሳቦችን ለማጥበብና ለማቀራረብ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም፣ ሀገራዊ የውይይት መድረክ እንዲፈጠር ተደርጓል፡፡ በዚህም ገና ከወዲሁ በርካታ ለዉጦች እየታዩ ሲሆን ውሳኔው ለምንመኛት የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን የማዕዘን ድንጋይ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ በአጠቃላይ መንግሥት መልአተ ሕዝቡን በማስተባበር ጠንካራና ብልጽግናዋን በልጆቿ ያረጋገጠች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እያደረገ ባለው ዘርፈ ብዙ ጥረት ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን የመፍጠርን ጉዳይ በልዩ ትኩረት የሚሰራበት ዋንኛው አጀንዳው ሆኖ ይቀጠላል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ
Dec 24, 2025 255
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 15/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ ገጽ ይፋ ሆኗል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን የዝግጅትን በ etaf90years.com ድረ-ገፅ አማካኝነት አጠቃላይ መረጃ ማግኘት እንደሚቻል ተቋሙ አስታውቋል። የምስረታ ቀን በዓሉ ላይ ኅብረተሰቡ እንዲሳተፍም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባወጣው መግለጫ ገልጿል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓሉን አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል:- ነሐሴ 12 ቀን 1921 ዓ.ም የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ የገባ ቢሆንም አየር ኃይላችን እንደ ተቋም አደረጃጀት ይዞ በይፋ የተመሰረተው ሕዳር 20 ቀን 1928 ዓ.ም ኢትዮጵያዊው ሻለቃ ሚሽካ ባብቼፍ የአየር ኃይል አዛዥ ሆነው በተመደቡበት ቀን ነው፡፡ ጀግናው የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90 ዓመታትን ባስቆጠረው የምስረታ ታሪኩ በየዘመናቱ ሁሉ የሀገርን ሉዓላዊነት በመጠበቅ አኩሪ ታሪክ ያለው ስመ ገናና ተቋም ነው፡፡አየር ኃይላችን የኢትዮጵያን የአየር ክልል በጀግንነት ከመጠበቅ ባሻገር በዓለም አቀፍ የሠላም ማስከበር ተልዕኮዎች በመሰማራት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ አውለብልቧል፡፡ የሠላም አምባሳደርነቱንም በተግባር አሳይቷል፡፡ በድል እና በመስዋዕትነት የደመቀ ታሪክም አኑሯል፡፡ በስልጠናው ዘርፍም ከራሱ አልፎ የሌሎች ሀገራት የአየር ኃይል ሙያተኞችን ማሰልጠኑን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ 90ኛ ዓመት የአየር ኃይል የምስረታ ቀን በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል ዋና መሪ ቃል ከጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድርስ በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድምቀት ይከበራል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር የጀመረ ሲሆን የዚሁ አካል የሆነውና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ቃል ሕዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ዓለም አቀፍ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በድምቀት ተካሂዷል፡፡ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ታላቅ አየር ኃይል እየተገነባ ነው -ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ይህ የሩጫ ውድድር ህብረተሰቡ በከፍተኛ መነቃቃት የተሳተፈበት፣ ተቋሙና ህዝቡ የተሳሰረበት፣የቱሪስት መዳረሻ የሆነችው ቢሾፍቱ ከተማ የተዋወቀችበት ከመሆኑም ባሻገር በቀጣይ ለሚካሄዱት ኩነቶች የአየር ኃይል የምስረታ ቀን ዋናው በዓል መሰረት ጥሎ ያለፈ ታሪካዊ ውድድር ነው፡፡ በመቀጠል ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ዓ.ም ጀምሮ የሚኖረው የሚከተሉትን ኩነቶች የያዘ ነው የመጀመሪያው በዓይነቱ ለየት ያለ እና ለሁለተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አየር ኃይል አዘጋጅነት ‘የአንበሶች ሠማይ! ኢትዮጵያ’ በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአየር ኃይል፣ የሩሽያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ የአየር ኃይል እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይል በጋራ የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት 2026 በድምቀት የሚካሄድ ይሆናል፡፡ በመቀጠል በከፍተኛ ጉጉት የሚጠበቀው "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የቻይና፣ የህንድ የአሜሪካ እና የደቡብ አፍሪካ ታላላቅ ኩባንያዎች ብሎም ከ 25 በላይ የሚሆኑ በአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት የአቪዬሽንና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ2026 ይካሄዳል፡፡ የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓል ከሚያከናውናቸው ኩነቶች አንዱ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦች የሚሳተፉበት እና "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ለ3ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አየር ኃይል አዘጋጅነት ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች በተገኙበት የሚካሄድ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ ከአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ጋር ያላትን ቅርብ ትስስር በተግባር የሚያረጋግጥ ይሆናል፡፡ አየር ኃይል የሀገርን ሉዓላዊነት በማስከበር አኩሪ ታሪክ አለው- ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓል ከሚካሄዱ መርሃ ግብሮች መካከል የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ የጦር አዛዦች እንዲሁም የሀገራችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል መሪ ቃል ከህብረተሰቡ ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ሕዝባዊ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ የበዓሉን የአከባበርን ሁኔታ የሚገልፅ እና የአየር ኃይልን ታሪክ የበለጠ የሚያሳውቅ፣ የዝግጅቱን ዝርዝር የሚያሳይ እንዲሁም የባለፉት ዓመታትን የተቋሙን የለውጥ ሂደት የሚያስቃኝና etaf90years.com የተሰኘ የኢቨንት ድረ ገፅ ያለው ሲሆን በዚሁ ድህረ ገፅ ሁሉንም የበዓሉ ኩነቶች ማግኘት የመግቢያ ቲኬት መግዛትና በድረ ገፅ ኩነቶቹን መከታተል ይቻላል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል በ90 ዓመት ጉዞው ለኢትዮጵያችን መስዋዕትነት ከፍሏል፡፡ የኢትዮጵያን የአየር ክልል በጀግንነት ጠብቋል፡፡ ሀገር አፅንቷል፤ ሀገር አሻግሯል፡፡ በእሳት ተፈትነው ያለፉ ብዙ ጀግኖችንም አፍርቷል፡፡ በውጊያ መሰረተ ልማት፣በሰው ኃይል ግንባታና ትጥቅ በማሟላት ኢትዮጵያን የሚመጥን ተቋም እየተገነባ ነው የከበረ እና የገዘፈ ታሪክ ያለው የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓሉን ሲያከብርም ያለፈውን ለመዘከር አሁናዊ የተቋሙን ቁመና ለማቀብ፣ የደረሰበትን ሁሉን አቀፍ ዝግጁነት ለማሳየት፣ የሀገራችንን ገጽታ በማጉላት እና የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ተስፋ ለማነሳሳት በሚያስችሉ ዝግጅቶች እንዲሁም ተግባራት የሚከበር መሆኑ ተመላክቷል። ኅብረተሰቡ በዓሉ ላይ እንዲገኝና በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባል ሆነው ያገለገሉትንና እያገለገሉ ያሉ ጀግኖችን እንዲያከብር፣ እንዲዘክር፣ የሀገር መመኪያና ኩራት የሆነው ተቋም እንዲመለከትና በዚህ አስደናቂና ታሪካዊ በዓል ላይ እንዲታደም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጥሪውን አቅርቧል፡፡
ልማት ላይ በመሳተፍ የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል - የቀድሞ ታጣቂዎች
Dec 24, 2025 218
መተማ፤ ታህሳስ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በሰላም ግንባታና ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል ሲሉ በምዕራብ ጎንደር ዞን የሰላም አማራጭን ተቀብለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች ገለጹ። በዞኑ መተማ ወረዳ ጉባይና ሌንጫ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ታጣቂዎቹ የሰላምን አማራጭ ተቀብለው ሲመለሱ ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት በማስረከብ ነው። ከተመላሾቹ መካከል ብርሃኑ አወቀ እና ስመኘው አዳነ፤ የተሳሳተ መንገድ ተከትለን በሕዝብ ላይ በፈጸምነው ጥፋት ተፀፅተናል ብለዋል። ግጭት በመፍጠር በአካባቢው ሕብረተሰብ በእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ ጫና ማሳደራችን ተገቢነት እንደሌላው ተገንዝበን ተመልሰናል ሲሉ ገልጸዋል። መንግስት ያመቻቸውን የሰላም እድል መምረጣቸውን ገልጸው፤ በጥፋታቸው በመፀፀት በቀጣይ በሰላም ግንባታና ልማት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህንንም ከመንግስትና ከሕብረተሰቡ ጎን በመሰለፍ በተግባር ለማረጋገጥ እንጥራለን ብለዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረሰ አዱኛ በበኩላቸው፤ ሰላምን ማፅናት ላይ ትኩረት ያደረጉ ሕዝባዊ ውይይቶች በተለያዩ የዞኑ አካባቢዎች ሲካሄዱ መቆየታቸውን ተናግረዋል። ከወይይቱ በኋላ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር ሕብረተሰቡ ድጋፉን ይበልጥ አጠናክሮ ሰላምን ለማፅናት በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መቻሉን ገልጸዋል። ወደ ሰላም የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችም የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ የቀሩትም እንዲመለሱ አሁንም የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል።
ወጣቶች የመደመር መንግስት እሳቤን እውን በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው
Dec 23, 2025 227
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ ወጣቶች የመደመር መንግስት እሳቤን እውን በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው የሲዳማ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። የሲዳማ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽንና ወጣቶቸ ማህበር “የተደመረ የወጣት አደረጃጀት ለሀገር ልማት እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ የምክክር ጉባኤ በሀዋሳ አካሂዷል። በጉባኤው የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ እመቤት ኢሳያስ እንዳሉት፤ ወጣቱ በክልሉም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት በሚደረገው ርብርብ ወጣቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል። ለዚህም በመደመር መንግስት እሳቤ የወጣቶችን አቅም በመገንባት ልማቱን ለማፋጠን ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል። የወጣቱን የስራ እድል ፈጠራ ለማሳደግም የክህሎት ስልጠናና የመስሪያና የመሸጫ እንዲሁም የብድር አገልግሎት አንዲያገኙ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የቢሮው ምክትልና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ለገሰ በበኩላቸው የክልሉ መንግስት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ የወጣቱን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማና በገጠር በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የወጣቱ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱንም ጠቁመዋል። የወጣቶች ፌዴሬሽንና ማህበር የጋራ ጉባኤው በመደመር እሳቤ ጠንካራ አደረጃጀት እንዲኖር ለማድረግና አመራሩን በአዲስ መልክ እንዲሰይም ታስቦ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። በጉባኤው የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆኖ የተመረጠው ወጣት ምንተስኖት መኩሪያ በበኩሉ ለሀገር ልማትና ሰላም ወጣቱ የነቃ የዜግነት ተሳትፎውን እንዲያሳድግ እንሰራለን ብሏል። በዚህም እንደ ወጣት ጠቃሚ ስራ በመስራት ለክልሉም ሆነ ለሀገር ብልጽግና ጉዞ መሳካት የድርሻውን ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን ጠቁሟል። የፌዴሬሽኑ አባል የሆነችው ወጣት ዘላለም ሰለሞን በበኩሏ የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንዲጎለብት ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስታውሳለች። ተግባሩንም በማስቀጠል ወጣቶች በሀገር ጉዳይ በንቃት እንዲሳተፉ በማስተባበር የበኩሏን እንደምትወጣም ገልጻለች። በጉባኤው የተለያዩ ክልሎች ፌዴሬሽን አመራሮች፣ ከሲዳማ ክልል አራት ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የወጣት ማህበራትና ፌዴሬሽን አደረጃጀቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።
ፖለቲካ
የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ
Dec 26, 2025 35
ባሕርዳር፤ ታሕሳስ 17/2018(ኢዜአ)፡ - የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ የተሻሻለውን የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን ጨምሮ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ። የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ በፌዴራል ደረጃ ተሻሽሎ ከፀደቀው ጋር እንዲጣጣም ተደርጎ የወጣ መሆኑም ተመላክቷል። የክልሉ መሬት ቢሮ ኃላፊ ሲሳይ ዳምጤ ለምክር ቤቱ እንደገለጹት፤ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል ነው። የገጠር መሬት ባለመብቶች መሬታቸውን ማከራየት፣ በዋስትና ማስያዝ፣ ከባለሃብቶች ጋር በጋራ ማልማትና በውርስ ወይም በስጦታ ለማስተላለፍ የሚፈቅድ እንደሆነ አስረድተዋል። አርሶ አደሩ የመሬት ይዞታ ዋስትና በመስጠት ያፈራውን ንብረት የመጠቀም መብትን ለማጠናከርና የገጠር መሬት ምዝገባ መረጃ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለማደራጀት የሚያስችል መሆኑንም አንስተዋል። እንዲሁም የሴቶችና ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን የመሬት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ አካታች የመሬት አጠቃቀም ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችልም አመልክተዋል። የምክር ቤቱ የግብርናና አካባቢ ጥበቃና ውሃ ሃብት ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከፍያለው ሙላቴ በበኩላቸው፤ የአዋጁ መፅደቅ ከመሬት ጋር ተያይዞ ይነሱ የነበሩ ችግሮችን በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ ጉባዔ በተጨማሪም የፕሮጀክት አስተዳደርና አመራር ስርዓት ፣ የኤክስሳይዝ ታክስን ለማሻሻል የወጣን አዋጅና የተሻሻለው የመንግስት ሰራተኞች አስተዳደርን ጨምሮ ሌሎች አዋጆች ላይ ተወያይቶ አፅድቋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ነው
Dec 25, 2025 180
ባሕርዳር ፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ) ፡- የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር፤ አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔ በባሕርዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፤ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በቅርቡ የተፈራረመው የዘላቂ ሰላም ስምምነት በክልሉ ሰላምን ለማፅናት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የክልሉ መንግስት ችግሮችን በውይይትና በንግግር መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲያቀርብ የነበረው የሰላም አማራጭ ፍሬ ማፍራቱን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል። ግጭት ይብቃ ብለው የክልሉን መንግስት የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለተመሰሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን ምክር ቤቱ ያመሰግናል ያሉት አፈ ጉባኤዋ ፤ ሌሎች በጫካ የቀሩ ታጣቂዎችም የሰላም ጥሪውን ተቀብለው እንዲመጡ ጠይቀዋል። የአማራ ክልል መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን ገልጸው ፤ አጠናክሮ እንዲቀጥል በምክር ቤቱ በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ትብብር የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክር ቤት አባላት ለመልካም አስተዳደር መስፈን፣ ለዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበርና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተያዘው ዓመት የሚካሄደው 7ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተአማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅና ህዝቡ በምርጫው በንቃት እንዲሳተፍ የምክር ቤት አባላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። ምክር ቤቱ የክልሉን ትምህርት ቢሮ የ5 ወራት እቅድ አፈፃፀምና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በተከናወኑ የፋይናንስ ህጋዊነትና ክዋኔ ኦዲት ግኝቶች ላይ እንደሚመክር ከመርሃ ግብሩ መረዳት ተችሏል። በጉባዔው ልዩ ልዩ አዋጆችና ሹመቶች እንደሚጸድቁም ይጠበቃል።
የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ ለውጦችን በሚያሳይ መልኩ ይከበራል
Dec 25, 2025 164
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ ከጥር 15 እስከ 19 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከበር በኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ ገለፁ። በበዓሉ ላይ "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በሚል የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብም ተመላክቷል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ፤ የአየር ኃይሉን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል መሪ ሃሳብ ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ደማቅ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር አስታውቀዋል። በበዓሉ ከጥር 15 ቀን ጀምሮ በሚካሄደውና "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በተሰኘው መርሃ ግብር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብ አመላክተዋል። በዚህም የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ የሩሲያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይሎች በጋራ በመሆን የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት እንደሚያቀርቡ ጠቅሰዋል። "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ የቻይና፣ ህንድ፣ አሜሪካ እና ደቡብ አፍሪካ ግዙፍ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ኤክስፖ እንደሚካሄድም ገልፀዋል። ከ25 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ የቴክኖሎጂ ተቋማት የደረሱበትን ደረጃ ለጉብኝት ክፍት የሚያደርጉበት "ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2026" እንደሚካሄድም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የአቪዬሽን ማዕከል መሆኗን የምታረጋግጥበት "ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም" ለሶስተኛ ጊዜ እንደሚካሄድም ተናግረዋል። "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው መድረክ ላይ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦችና ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች ይታደማሉ ነው ያሉት። የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አዛዦችና የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል ርዕስ ከህዝቡ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ጠቅሰዋል። በዓሉ የአየር ኃይሉን የ90 ዓመት የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በማሳየት ይከበራል ነው ያሉት። መላው የሀገሪቱ ህዝብ በዚህ ታሪካዊ በዓል ላይ በመገኘት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የደረሰበትን ዝግጁነት እንዲመለከት ጥሪ አቅርበዋል። የበዓሉ አካል የሆነና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ሃሳብ ባሳለፍነው ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ የ10 ኪሎ ሜትር ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ሩጫ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይህ ውድድር በህዝብና በተቋሙ መካከል ያለውን ትስስር ያጠናከረና ለዋናው በዓል መሰረት የጣለ ታሪካዊ ኹነት ሆኖ ማለፉንም ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
Dec 25, 2025 121
ባሕር ዳር፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔውን መካሄድ ጀምሯል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ የአምስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለጉባዔው ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል። በውይይቱ በትምህርት አጀማመርና በተከናወኑ ተግባራት ላይ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ተጠቁሟል። እንዲሁም በክልሉ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የፋይናንስ ሕጋዊነትና የክዋኔ ኦዲት ግኝቶችንና የተሰጡ የማሻሻያ ሐሳቦችን የሚያሳይ የተጠቃለለ ሪፖርት ላይ እንደሚመክር ተመላክቷል። ጉባዔው ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፤ በቆይታው ልዩ ልዩ ዐዋጆች እና ሹመቶችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።
መንግሥት ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል-የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Dec 24, 2025 208
አዲስ አበባ፣ታኅሣስ 15/2018(ኢዜአ)፡-መንግሥት የሀገር ግንባታ ሂደቱን ለማጽናት እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል፡፡ እነዚህ ሦስቱ ምሰሶዎች ሀገራዊ አንድነትን፣ሰላምና ብልጽግናን፣ እንዲሁም ዜጎች በመተማመን እና በተጠያቂነት ላይ የተመሠረተ የጋራ ራዕይ እንዲኖራቸዉ የሚያደርጉ ቁልፍ መሰረቶች ናቸው፡፡ ዲሞክራሲን የመገንባት ሂደት ለአንድ ሀገር ወሳኝ ተግባር ሲሆን፣ በዋናነት ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቁ ተቋማትን ማቋቋም ላይ ትኩረት ያደረገ ነዉ፡፡ተቋማቱ የሚመሩባቸዉ ህጎችና የአሰራር ሥርዓቶች፣የተቋማቱ አወቃቀርና አደረጃጀት፣ እንዲሁም ለህዝብ ያላቸዉን ተዓማኒነትን መጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራበት ይገኛል፡፡ ጠንካራ የዲሞክራሲ ባህልና ሥርዓት የሚገነባው ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት ሲፈጠሩና ሲጠናከሩ መሆኑን መንግሥት በጽኑ የሚገነዘበው ጉዳይ ነዉ፡፡በዚህም ኢትዮጵያ ባለፉት 7 ዓመታት በዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ሂደት ውስጥ ሁለተናዊ ሪፎርም ሥራዎችን ስታከናውን ቆይታለች፡፡ እነዚህ ሪፎርሞች የሀገሪቱን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑትን የዲሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እና ጠንካራ አድርጎ ለመገንባት መንግሥት ምን ያህል ቁርጠኛ እንደሆነ ያሳየባቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ተቋማት መጠናከር በአንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም እና ልማት እንዲረጋገጥ እንደ ዋንኛ ምሰሶ የሚወሰድ ነው፡፡ በተለይም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ የታዩ ተጨባጭ ለውጦች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ለመጠበቅ፣ እንዲሁም የሕዝቡን ዕምነት ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ መንግሥት በተለይ ተቋማዊ ዐቅምን በማሳደግ እና ነፃነትን በማረጋገጥ፣ የዲሞክራሲ ምህዳርን እንዲሰፋ ለማደረግ የሚጠበቅበት ግዴታ ብቻ ሳይሆን ዲሞክራሲ የሚያብብበትን አስቻይ ዐውድና ማዕቀፍ ለመፍጠር ዓለማው አድረጓል፡፡ ይሄንን ከግብ ለማድረስ በተለይ የፀጥታ፣ የፍትሕ፣ የሲቪልና የሚዲያ ተቋማት፣ እንዲሁም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕዝብን ማዕከል አድርገው እንዲሰሩ መንግሥት በቁርጠኝነት በመደገፉ እንደ ሀገር ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ በማደርረግ ተጨባጭ ዉጤቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል፡፡ ሌላው መንግስት በትኩረት እየሰራበት ያለው ጉዳይ እንደ ሀገር ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ነዉ፡፡ ይህ ሂደት ዋና ዓለማ ያደረገው መላዉ ሕዝብ፣ ተቋማት፣ አመራርና ሠራተኛዉ በሀገራዊ ራዕይ ላይ በተለያዩ ድምጾች የጋራ እድገትን በመገንባት ሀገራዊ ህለውና እና ብልጽግና እንዲረጋገጥ እንዲሁም በዜጎች መካከል መተማመን እና ሀገራዊ አንድነትን እንዲፈጠር ማድርግ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ የብዙሃን ድምጽ የሚሰማበት የፖለቲካ ዐዉድ ለመፍጠር አያሌ የፖለቲካ ማሻሻያዎችን አድርጋለች፡፡ በዚህም እስከዛሬ በነበሩ መንግሥታት ያለተሞከረውን ጫፍ ወጥተው የሚታዩ ተቃርኖ ሀሳቦችን ለማጥበብና ለማቀራረብ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም፣ ሀገራዊ የውይይት መድረክ እንዲፈጠር ተደርጓል፡፡ በዚህም ገና ከወዲሁ በርካታ ለዉጦች እየታዩ ሲሆን ውሳኔው ለምንመኛት የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን የማዕዘን ድንጋይ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ በአጠቃላይ መንግሥት መልአተ ሕዝቡን በማስተባበር ጠንካራና ብልጽግናዋን በልጆቿ ያረጋገጠች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እያደረገ ባለው ዘርፈ ብዙ ጥረት ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን የመፍጠርን ጉዳይ በልዩ ትኩረት የሚሰራበት ዋንኛው አጀንዳው ሆኖ ይቀጠላል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ
Dec 24, 2025 255
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 15/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ ገጽ ይፋ ሆኗል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን የዝግጅትን በ etaf90years.com ድረ-ገፅ አማካኝነት አጠቃላይ መረጃ ማግኘት እንደሚቻል ተቋሙ አስታውቋል። የምስረታ ቀን በዓሉ ላይ ኅብረተሰቡ እንዲሳተፍም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ባወጣው መግለጫ ገልጿል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓሉን አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል:- ነሐሴ 12 ቀን 1921 ዓ.ም የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ የገባ ቢሆንም አየር ኃይላችን እንደ ተቋም አደረጃጀት ይዞ በይፋ የተመሰረተው ሕዳር 20 ቀን 1928 ዓ.ም ኢትዮጵያዊው ሻለቃ ሚሽካ ባብቼፍ የአየር ኃይል አዛዥ ሆነው በተመደቡበት ቀን ነው፡፡ ጀግናው የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90 ዓመታትን ባስቆጠረው የምስረታ ታሪኩ በየዘመናቱ ሁሉ የሀገርን ሉዓላዊነት በመጠበቅ አኩሪ ታሪክ ያለው ስመ ገናና ተቋም ነው፡፡አየር ኃይላችን የኢትዮጵያን የአየር ክልል በጀግንነት ከመጠበቅ ባሻገር በዓለም አቀፍ የሠላም ማስከበር ተልዕኮዎች በመሰማራት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ አውለብልቧል፡፡ የሠላም አምባሳደርነቱንም በተግባር አሳይቷል፡፡ በድል እና በመስዋዕትነት የደመቀ ታሪክም አኑሯል፡፡ በስልጠናው ዘርፍም ከራሱ አልፎ የሌሎች ሀገራት የአየር ኃይል ሙያተኞችን ማሰልጠኑን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ 90ኛ ዓመት የአየር ኃይል የምስረታ ቀን በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል ዋና መሪ ቃል ከጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድርስ በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድምቀት ይከበራል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር የጀመረ ሲሆን የዚሁ አካል የሆነውና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ቃል ሕዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ዓለም አቀፍ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በድምቀት ተካሂዷል፡፡ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ታላቅ አየር ኃይል እየተገነባ ነው -ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ይህ የሩጫ ውድድር ህብረተሰቡ በከፍተኛ መነቃቃት የተሳተፈበት፣ ተቋሙና ህዝቡ የተሳሰረበት፣የቱሪስት መዳረሻ የሆነችው ቢሾፍቱ ከተማ የተዋወቀችበት ከመሆኑም ባሻገር በቀጣይ ለሚካሄዱት ኩነቶች የአየር ኃይል የምስረታ ቀን ዋናው በዓል መሰረት ጥሎ ያለፈ ታሪካዊ ውድድር ነው፡፡ በመቀጠል ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ዓ.ም ጀምሮ የሚኖረው የሚከተሉትን ኩነቶች የያዘ ነው የመጀመሪያው በዓይነቱ ለየት ያለ እና ለሁለተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አየር ኃይል አዘጋጅነት ‘የአንበሶች ሠማይ! ኢትዮጵያ’ በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአየር ኃይል፣ የሩሽያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ የአየር ኃይል እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይል በጋራ የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት 2026 በድምቀት የሚካሄድ ይሆናል፡፡ በመቀጠል በከፍተኛ ጉጉት የሚጠበቀው "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ አየር ኃይል፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የቻይና፣ የህንድ የአሜሪካ እና የደቡብ አፍሪካ ታላላቅ ኩባንያዎች ብሎም ከ 25 በላይ የሚሆኑ በአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት የአቪዬሽንና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ2026 ይካሄዳል፡፡ የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓል ከሚያከናውናቸው ኩነቶች አንዱ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦች የሚሳተፉበት እና "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ለ3ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አየር ኃይል አዘጋጅነት ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች በተገኙበት የሚካሄድ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ ከአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ጋር ያላትን ቅርብ ትስስር በተግባር የሚያረጋግጥ ይሆናል፡፡ አየር ኃይል የሀገርን ሉዓላዊነት በማስከበር አኩሪ ታሪክ አለው- ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓል ከሚካሄዱ መርሃ ግብሮች መካከል የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ የጦር አዛዦች እንዲሁም የሀገራችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል መሪ ቃል ከህብረተሰቡ ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ሕዝባዊ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ የበዓሉን የአከባበርን ሁኔታ የሚገልፅ እና የአየር ኃይልን ታሪክ የበለጠ የሚያሳውቅ፣ የዝግጅቱን ዝርዝር የሚያሳይ እንዲሁም የባለፉት ዓመታትን የተቋሙን የለውጥ ሂደት የሚያስቃኝና etaf90years.com የተሰኘ የኢቨንት ድረ ገፅ ያለው ሲሆን በዚሁ ድህረ ገፅ ሁሉንም የበዓሉ ኩነቶች ማግኘት የመግቢያ ቲኬት መግዛትና በድረ ገፅ ኩነቶቹን መከታተል ይቻላል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል በ90 ዓመት ጉዞው ለኢትዮጵያችን መስዋዕትነት ከፍሏል፡፡ የኢትዮጵያን የአየር ክልል በጀግንነት ጠብቋል፡፡ ሀገር አፅንቷል፤ ሀገር አሻግሯል፡፡ በእሳት ተፈትነው ያለፉ ብዙ ጀግኖችንም አፍርቷል፡፡ በውጊያ መሰረተ ልማት፣በሰው ኃይል ግንባታና ትጥቅ በማሟላት ኢትዮጵያን የሚመጥን ተቋም እየተገነባ ነው የከበረ እና የገዘፈ ታሪክ ያለው የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን በዓሉን ሲያከብርም ያለፈውን ለመዘከር አሁናዊ የተቋሙን ቁመና ለማቀብ፣ የደረሰበትን ሁሉን አቀፍ ዝግጁነት ለማሳየት፣ የሀገራችንን ገጽታ በማጉላት እና የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ተስፋ ለማነሳሳት በሚያስችሉ ዝግጅቶች እንዲሁም ተግባራት የሚከበር መሆኑ ተመላክቷል። ኅብረተሰቡ በዓሉ ላይ እንዲገኝና በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባል ሆነው ያገለገሉትንና እያገለገሉ ያሉ ጀግኖችን እንዲያከብር፣ እንዲዘክር፣ የሀገር መመኪያና ኩራት የሆነው ተቋም እንዲመለከትና በዚህ አስደናቂና ታሪካዊ በዓል ላይ እንዲታደም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጥሪውን አቅርቧል፡፡
ልማት ላይ በመሳተፍ የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል - የቀድሞ ታጣቂዎች
Dec 24, 2025 218
መተማ፤ ታህሳስ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በሰላም ግንባታና ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል ሲሉ በምዕራብ ጎንደር ዞን የሰላም አማራጭን ተቀብለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች ገለጹ። በዞኑ መተማ ወረዳ ጉባይና ሌንጫ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ታጣቂዎቹ የሰላምን አማራጭ ተቀብለው ሲመለሱ ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት በማስረከብ ነው። ከተመላሾቹ መካከል ብርሃኑ አወቀ እና ስመኘው አዳነ፤ የተሳሳተ መንገድ ተከትለን በሕዝብ ላይ በፈጸምነው ጥፋት ተፀፅተናል ብለዋል። ግጭት በመፍጠር በአካባቢው ሕብረተሰብ በእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ ጫና ማሳደራችን ተገቢነት እንደሌላው ተገንዝበን ተመልሰናል ሲሉ ገልጸዋል። መንግስት ያመቻቸውን የሰላም እድል መምረጣቸውን ገልጸው፤ በጥፋታቸው በመፀፀት በቀጣይ በሰላም ግንባታና ልማት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህንንም ከመንግስትና ከሕብረተሰቡ ጎን በመሰለፍ በተግባር ለማረጋገጥ እንጥራለን ብለዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረሰ አዱኛ በበኩላቸው፤ ሰላምን ማፅናት ላይ ትኩረት ያደረጉ ሕዝባዊ ውይይቶች በተለያዩ የዞኑ አካባቢዎች ሲካሄዱ መቆየታቸውን ተናግረዋል። ከወይይቱ በኋላ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር ሕብረተሰቡ ድጋፉን ይበልጥ አጠናክሮ ሰላምን ለማፅናት በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መቻሉን ገልጸዋል። ወደ ሰላም የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎችም የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ የቀሩትም እንዲመለሱ አሁንም የሰላም በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል።
ወጣቶች የመደመር መንግስት እሳቤን እውን በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን ማጠናከር አለባቸው
Dec 23, 2025 227
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦ ወጣቶች የመደመር መንግስት እሳቤን እውን በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው የሲዳማ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። የሲዳማ ክልል ወጣቶች ፌዴሬሽንና ወጣቶቸ ማህበር “የተደመረ የወጣት አደረጃጀት ለሀገር ልማት እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ የምክክር ጉባኤ በሀዋሳ አካሂዷል። በጉባኤው የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ እመቤት ኢሳያስ እንዳሉት፤ ወጣቱ በክልሉም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት በሚደረገው ርብርብ ወጣቶች ሚናቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል። ለዚህም በመደመር መንግስት እሳቤ የወጣቶችን አቅም በመገንባት ልማቱን ለማፋጠን ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል። የወጣቱን የስራ እድል ፈጠራ ለማሳደግም የክህሎት ስልጠናና የመስሪያና የመሸጫ እንዲሁም የብድር አገልግሎት አንዲያገኙ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የቢሮው ምክትልና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ለገሰ በበኩላቸው የክልሉ መንግስት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ የወጣቱን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማና በገጠር በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የወጣቱ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱንም ጠቁመዋል። የወጣቶች ፌዴሬሽንና ማህበር የጋራ ጉባኤው በመደመር እሳቤ ጠንካራ አደረጃጀት እንዲኖር ለማድረግና አመራሩን በአዲስ መልክ እንዲሰይም ታስቦ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። በጉባኤው የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆኖ የተመረጠው ወጣት ምንተስኖት መኩሪያ በበኩሉ ለሀገር ልማትና ሰላም ወጣቱ የነቃ የዜግነት ተሳትፎውን እንዲያሳድግ እንሰራለን ብሏል። በዚህም እንደ ወጣት ጠቃሚ ስራ በመስራት ለክልሉም ሆነ ለሀገር ብልጽግና ጉዞ መሳካት የድርሻውን ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን ጠቁሟል። የፌዴሬሽኑ አባል የሆነችው ወጣት ዘላለም ሰለሞን በበኩሏ የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንዲጎለብት ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስታውሳለች። ተግባሩንም በማስቀጠል ወጣቶች በሀገር ጉዳይ በንቃት እንዲሳተፉ በማስተባበር የበኩሏን እንደምትወጣም ገልጻለች። በጉባኤው የተለያዩ ክልሎች ፌዴሬሽን አመራሮች፣ ከሲዳማ ክልል አራት ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የወጣት ማህበራትና ፌዴሬሽን አደረጃጀቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።
ማህበራዊ
የሐይማኖት አባቶች ለአብሮነት መጎልበት ከመቼውም ጊዜ በላይ የላቀ ሚናቸውን እንደሚወጡ ገለጹ
Dec 26, 2025 21
ባሕር ዳር፤ ታኅሣስ 17/2018 (ኢዜአ)፡- ለሀገር ሰላም፣ ፍቅርና አብሮነት መጎልበት የላቀ ሚናችንን መወጣታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የተለያዩ የሐይማኖት አባቶች ተናገሩ። ''ዘካሪ መካሪ የሐይማኖት አባት ለዘላቂ ሰላምና ልማት'' በሚል መሪ ሐሳብ ከሰሜን ጎጃም ዞን የተውጣጡ የተለያዩ የሐይማኖት አባቶች የተሳተፉበት መድረክ በባሕር ዳር ከተማ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት የመድረኩ ተሳታፊዎች ለሀገር ሰላምና ልማት መጎልበት የሀገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶች ሚና የላቀ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። የሰላም ግንባታ ሂደት ያለ ሐይማኖታዊና የሞራል ዕሴቶች ስኬታማ ስለማይሆን እነዚህን ለማስጠበቅ አጠቃላይ ምዕመኑንና ወጣቶችን ማስተማር ይገባል ብለዋል። በክልሉ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሐይማኖት አባቶች ሚናቸውን ይበልጥ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ቄስ ታዘበው ጌታሁን በሰጡት አስተያየት፤ የሰላም መታጣት በተለያዩ አካባቢዎች ሁላችንንም ዋጋ እያስከፈለን በመሆኑ ከምንም በላይ ለሰላም ዘብ መቆም ይገባናል ብለዋል። የሰላም ግንባታ ከግለሰብ ጀምሮ ወደ ቤተሰብና ሀገር የሚዘልቅ በመሆኑ እያንዳንዱ ግለሰብ ስለ ሰላም አደራና ኃላፊነት ያለበት መሆኑንም አስገንዝበዋል። ሼኽ ሙሐመድ አደም በበኩላቸው፤ የሰላም ጉዳይ የእያንዳንዳችን ጥረትና ትጋት ውጤት በመሆኑ ሁላችንንም ይመለከተናል ብለዋል። የጥፋት እንቅስቃሴን በማውገዝና ከጥፋት እንዲመለሱ በመምከር ጭምር የሰላም ዕሴቶች እንዲጎለብቱ በተለይም የሐይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የላቀ ሚናችንን መወጣት አለብን ሲሉ ተናግረዋል። የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አሰፋ ጥላሁን፤ የሐይማኖቶች ዕሴቶች ሰላምን፣ ፍቅርን፣ አንድነትን፣ ይቅርታንና መልካምነትን የሚሰብኩ በመሆኑ የአባቶች ትምህርት ትልቅ ትርጉም እንዳለው አንስተዋል። በመሆኑም የሐይማኖት አባቶች አጥፊዎችን መክሮ በመመለስ፣ በመልካም ተግባራት የተሰማሩትን በማመሥገን ለሰላም ዕሴቶች ግንባታ የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የሐይማኖት አባቶች የሰላም ጠባቂ፣ መካሪና አስታራቂ በመሆን የጀመሩትን ሥራ መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በክልሉ የተፈጠረውን ችግር በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት መንግሥት ብዙ መሥራቱን አስታውሰው በቀጣይም አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። በአንጻሩ የሰላም ጥሪ በመግፋት በጥፋት የሚቀጥሉ አካላት ላይ መንግሥት የተጠናከረ ርምጃ በመውሰድ ሕግ የሚያስከብር መሆኑንም ነው ያስታወቁት።
መገናኛ ብዙሃን ብሔራዊ ትርክትን ለመገንባት ቅድሚያ ሰጥተው መስራት ይጠበቅባቸዋል
Dec 26, 2025 34
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦መገናኛ ብዙሃን የሀገር ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርና የብሔራዊነት ትርክትን ለመገንባት ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ ገለጹ። 48ኛው የ"ጉሚ በለል" የውይይት መድረክ "ብሔራዊ ጥቅም እና መገናኛ ብዙሃን" በሚል መሪ ሐሳብ በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ተካሂዷል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ በዚሁ ወቅት፤ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም በትውልድ የማይገደብ መሆኑን ገልጸዋል። መገናኛ ብዙሃንም ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው ገልጸው፤ የሕዝብ አንድነትን ለማጠናከር እንዲሁም የኢትዮጵያን ተደማጭነት ለማሳደግ ግንባር ቀደም ሚናቸውን መወጣት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። ለብሔራዊ ትርክት ግንባታ እና ሐሰተኛ መረጃን ለመከላከል በትኩረት መሥራት እንዳለባቸውም ተናግረዋል። የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ጥረት ግንባር ቀደም መሆን እንዳለባቸው ጠቁመው፤ ለአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮችም ትኩረት መስጠት ይገባቸዋል ብለዋል። የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ እንደገለጹት፤ መገናኛ ብዙሃን ብሔራዊ ጥቅም ከማስጠበቅ አኳያ የማይተካ ሚና አላቸው። ስለሆነም መገናኛ ብዙሃን ለሀገር እና ሕዝብ ጥቅም ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው ነው ያመለከቱት። መገናኛ ብዙሃን ለገጽታ ግንባታ ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ኃይሉ፤ በጎ ገጽታን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማስተዋወቅ ረገድ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆናቸውን አመልክተዋል። ለዚህ ስኬት ዘመኑን የዋጁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መታጠቅ እንዲሁም የሰለጠነ የሰው ሃይል ማሟላት እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየትም መገናኛ ብዙሃን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበርና ሉዓላዊነት መጠበቅ ሚናችንን እናጠናከራለን ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተፈራ በቀለ፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ የመገናኛ ብዙሃን ቀዳሚ ተግባር መሆን ይገባዋል ብለዋል፡፡ ከዚህም አኳያ ኢዜአ የሀገርን ገጽታ የሚገነቡ፣ ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ እንዲሁም ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎችን በግንባር ቀደምትነት እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቢንያም ኤሮ፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ ከምንም በፊት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ ተቋማቸው ብሔራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ የይዘት ስራዎችን በመሥራት የብሔራዊ ትርክትን ለመገንባት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አድማሱ ዳምጠው፤ መገናኛ ብዙሃን በተደመረ አቅም ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር በጋራ መትጋት አለባቸው ብለዋል፡፡ የኤን ቢሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዋና ስራ አስፈጻሚ ብሩክ ከበደ በበኩላቸው፤ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ከሀገር ብሔራዊ ጥቅም አኳያ ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ስልጠና እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። የኦቢኤን ዋና ዳይሬክተር አቶ ፍሰሃ በላይነህ ፤ መገናኛ ብዙሃን ማስገንዘብ፣ የማጋለጥ እና የመከላከል ሚናውን ማጠናከር አለበት ብለዋል፡፡ በኦሮሚያ ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት እና በኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ትብብር የሚዘጋጀው የ"ጉሚ በለል" መድረክ በተለያዩ ወቅታዊና ስትራቴጂካዊ ሀገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ምሁራንና የሥራ ኃላፊዎች የሚወያዩበት መድረክ ነው።
የአመራር ክኅሎትን በማሳደግ የጤና አገልግሎት ሥርዓትን ለማሳለጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይጠናከራሉ
Dec 26, 2025 24
ሠመራ፤ ታኅሣስ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በጤናው ዘርፍ የአመራር ክኅሎትን በማሳደግ የጤና አገልግሎት ሥርዓትን ለማሳለጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። በአፋር ክልል የጤና ሥርዓቱን በዘመናዊ የአሥተዳደር ሥርዓት ለመምራት የሚያስችል ተከታታይና ተግባር ተኮር ሥልጠና የተከታተሉ 80 የጤና ባለሙያዎች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ በሠመራ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ሳሀረላ አብዱላሂ እንዳሉት፤ የጤና ባለሙያውን ክኅሎት በሥልጠና ማሳደግ ሚኒስቴሩ በትኩረት ከያዛቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ ነው። በዚህም መሠረት በጤናው ዘርፍ የአመራር ክኅሎትን በማሳደግ የጤና አገልግሎት ሥርዓትን ለማሳለጥ ሚኒስቴሩ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። ሚኒስቴሩ የተለያዩ መርሐ-ግብሮችን በመንደፍ በርካታ ሥራዎችን ሲሠራ መቆየቱን ገልፀው፤ በጤናው ዘርፍ የአመራር ክኅሎት ለማሳደግ እንዲቻል የተሰጠው ሥልጠናም የዚሁ አካል ነው መሆኑን አስታውቀዋል። ሰልጣኞች ከሥልጠናው የቀሰሙትን ዕውቀት በቀጣይ ሌሎችን በማብቃት ሚናቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ያሲን ሀቢብ በበኩላቸው፤ ሰልጣኞች በጤና ተቋማት ውስጥ የተሻለ ሥራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ተግባር ተኮር ሥልጠና መውሰዳቸውን ጠቁመዋል። የጤና ባለሙያዎቹ በሥልጠናው በመታገዝ ጠንካራ የጤና ሥርዓትን በመተግበር የተሳለጠ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል። የጤና ሥርዓቱን ለማሻሻል ባለሙያዎችን ለማብቃት የሚደረገውን ጥረት አድንቀው፤ ማኅበሩ የበኩሉን ለማገዝ ጥረት ያደርጋል ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዚዳንት ዶክተር ዓለማየሁ መኮንን ናቸው። ከገዋኔ፣ ጭፍራና ተላላክ ወረዳዎች ከሚገኙ ሆስፒታሎች፣ ጤና ጣቢያዎችና ጽሕፈት ቤቶች የተውጣጡ 80 የጤና ባለሙያዎች ሥልጠናውን መውሰዳቸው ተገልጿል።
በሀገር ክብርና ጥቅም ቀይ መስመር ሊኖረን ይገባል- ዑስታዝ አቡበከር አህመድ
Dec 26, 2025 38
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ክብርና ብሔራዊ ጥቅሞች ላይ የጋራ አቋም መያዝ እንደሚገባ የእስልምና ሃይማኖት አስተምህሮ መምህሩ ዑስታዝ አቡበከር አህመድ ገለጹ። ሀገርን በመግባባትና ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን እንደ ታሪካዊ ዕድል መጠቀም እንደሚገባ አንስተዋል። የአንድ ሀገር ሕልውና በማህበረሰቡ የአብሮነት፣ የመቻቻልና የጋርዮሽ እሴቶች ላይ የተመሰረተ መሆኑ ዕሙን ነው። ግብረ ገብነትና የማህበረሰብ መስተጋብር መሰረት የሆኑ እሴቶች መሸርሸር ደግሞ የማህበረሰቡን ሰላም ከማናጋት፣ ቅራኔ ከመፍጠር ባሻገር የሀገር ቀጣይነትና ብሔራዊ ጥቅም ሳንካ ይሆናል። ዕውቁ የእስልምና ሃይማኖት አስተምህሮ መምህር ዑስታዝ አቡበከር አህመድ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የኢትዮጵያን ማህበራዊ እሴቶችና ህጸጾች፣ ማህበራዊ ሚዲያ፣ ምክክርና ብሄራዊ ጥቅሞችን አስተሳስረው አብራርተዋል። ሚዲያ ትውልድን ለማነጽና ለሀገር ገጽታ አይተኬ ሚና ቢኖረውም በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ በተለይም የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ልቅ እና ያልተገራ በመሆኑ ከጥቅሙ ጉዳቱ እያመዘነ እንደሆነ ያምናሉ። ሚዲያ በቅጡ ካልተመራ ከዕድል ይልቅ ስጋቱ ያመዘነ፣ የማህበረሰባዊ መስተጋብር፣ የአብሮነትና የሰላም መሰረት የሆኑ እሴቶችን የሚያናጋ በመሆኑ መስመር ማበጀት እንደሚሻ ገልጸዋል። ቻይናን መሰል ሀገራት ሀገራዊ እሴቶችን የሚንዱ ማህበራዊ ሚዲያዎችን ከመቆጣጠር ባሻገር በራሳቸው ቅኝት እንዲመሩ ማድረጋቸውን በማውሳት መንግሥት በዚህ ረገድ ያለውን ወሳኝ ሚና ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ውስጥ ከባህልና ከሃይማኖት ያፈነገጡ የማህበራዊ ሚዲያ ይዘቶች መበራከት የሃይማኖት ተቋማት በትውልድ ስነ ምግባር ላይ በአግባቡ እንዳልሰሩ ሁነኛ ማሳያ እንደሆነ ጠቁመዋል። በማህበራዊ ሚዲያ የሚስተዋሉ አሉታዊ መልኮች ከየትኛውም ሃይማኖታዊ አስተምህሮ ያፈነገጡ መሆናቸውን በመጠቆም፣ የእምነት ተቋማትና ልሂቃን በግልም ሆነ በጋራ ተቋማት በኩል ትውልድ ግንባታ ላይ አበክረው መስራት እንደሚገባቸው ነው ያነሱት። ሀገር የጋራ ነው ያሉት ዑስታዝ አቡበከር፤ የሀገርን መሰረትና መገለጫዎቿን የሚጻረሩ አካሄዶችን የማረም፣ ትውልድ የመቅረጽ፣ የማነጽና የመገሰጽ ኃላፊነት የሁላችንም ነው ብለዋል። ከነባር ኢትዮጵያዊ እሴቶች መካከል መረዳዳትን እንደ አብነት አንስተው፤ ማህበራዊ ሚዲያን ለዚህ በጎ እሴት በአግባቡ የሚጠቀሙ ግለሰቦችና ተቋማት እንዳሉ አልሸሸጉም። በአንጻሩ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ኢ-ስነ ምግባራዊና ኢ-ሃይማኖታዊ የሆኑ ማህበረሰብን የማታለል አካሄዶች በስፋት እንደሚስተዋሉ በማውሳት ተችተዋል። የጋራችን የሆነች ኢትዮጵያን የጋራ የአብሮነት እሴቶችን ማጎልበት፣ ሲንከባለሉ የቆዩ የልዩነት ትርክቶችን ለማረቅ ደግሞ መወያየትና መመካከርን እንደ ሁነኛ አማራጭ አንስተዋል። በዚህ ረገድ ሀገራዊ የምክክር ሂደት መጀመሩ የዚህ ትውልድ ታሪካዊ ዕድል መሆኑን በማንሳት፤ በምክክር ሂደቱ በመሳተፍ ለስኬታማነቱ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ሀገራዊ ጥቅሞችና ጉዳዮች ለግል ጥቅምና ፍላጎት መሸጥ እንደሌለባቸው በማንሳት፤ ከብሔራዊ ጥቅሞች በተቃርኖ መቆም የሀገር ክህደት ነው ብለዋል። ለሀገር ክብር፣ ጥቅምና ገጽታ ቀይ መስመር ማበጀት እንደሚያሻም ነው ዑስታዝ አቡበከር ያስገነዘቡት።
ኢኮኖሚ
በነቀምቴ ከተማ ለወጣቶች በተፈጠረ የስራ እድል በርካቶች ተጠቃሚ እየሆኑ ነው
Dec 26, 2025 36
ነቀምቴ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦በነቀምቴ ከተማ በሌማት ትሩፋት ኢንዱስትሪና ሌሎችም ዘርፎች ለወጣቶች በተፈጠረ የስራ እድል በርካቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን የከተማዋ የስራ እድል ፈጠራ እና ክህሎት ፅህፈት ቤት አስታወቀ። የነቀምቴ ከተማ የስራ እድል ፈጠራ እና ክህሎት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ብርሀኑ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤በበጀት ዓመቱ ለ14 ሺህ 560 የከተማዋ ወጣቶች በተለያዩ ዘርፎች የስራ እድል የመፍጠር እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው። በተለይም በአግሮ ኢንዱስትሪ፣ በጨረቃ ጨርቅ፣ በእንስሳት እርባታ፣ በግብርና እና ሌሎችም ዘርፎች ወጣቶች እንዲሰማሩ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በመሆኑም በበጀት ዓመቱ እስካሁን በእነዚህና ሌሎችም ዘርፎች ወጣቶች እየሰሩ እራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ተጠቃሚ እያደረጉ ይገኛሉ ብለዋል። እየሰሩ በመጠቀምና በመቆጠብ ጭምር የወደፊት የኢኮኖሚ አቅማቸውን ለማሳደግ የሚጥሩ በርካቶች መሆናቸውን አንስተው እስካሁን ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ስለመቆጠባቸው ጠቅሰዋል። በነቀምቴ ከተማ በሌማት ትሩፋት ኢንዱስትሪና ሌሎችም ዘርፎች ለብዙ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን የገለጹት ኃላፊው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች በበኩላቸው፤በተሰማሩባቸው የስራ ዘርፎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአያና እና ሲምቦ የሽርክና ማህበር ሰብሳቢ ወጣት ኬና አያና፤ ከሁለት አመት በፊት በተሰማሩበት የጨርቃጨርቅ ምርት ስኬታማ በመሆን ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች ወጣቶችም የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግሯል። በድርጅቱ የስራ እድል ተጠቃሚ ከሆኑት ወጣቶች መካከል ቆንጂት በንቲ፤ በስራው ገቢ ከማግኘት ባለፈ ለቀጣይ ህይወቷ የሚጠቅም እውቀትና ክህሎት እያካበተች መሆኑን ገልፃለች። በተገኘው የስራ እድል አሁን ላይ ከራሷ አልፋ ቤተሰቦቿን እያገዘች መሆኑንም ተናግራለች። በአካባቢው እየተፈጠረ ባለው የስራ እድል በርካታ ወጣቶች ወደ ስራ እየገቡና ተጠቃሚ እየሆኑ መሆኑንም ገልጻለች።
የተፈጠረልን የሥራ ዕድል ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ባሻገር በዘርፉ እውቀት እንድንቀስም እያገዘን ነው- ወጣቶች
Dec 26, 2025 40
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦ በተመረቁበት የሙያ መስክ መሰማራታቸው ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ባለፈ ለነገ ስንቅ የሚሆን ተግባራዊ እውቀት እንዲያገኙ ማስቻሉን በባህር ዳር ከተማ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች ገለጹ። በበጀት ዓመቱ አምስት ወራት ብቻ በባህር ዳር ከተማ በኢንዱስትሪ ዘርፉ ስምንት ሺህ ለሚደርሱ ወጣቶች ቋሚ የሥራ ዕድል መፈጠሩ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ለኢንዱስትሪው ዘርፍ በሰጠችው ከፍተኛ ትኩረት በርካታ የኢንዱስትሪ ፓርኮችንና ፋብሪካዎችን መገንባት ችላለች። ኢንዱስትሪዎቹ ምርቶቻቸውን ወደ ውጪ በመላክ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከማሳደጋቸውም በላይ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልና የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፈጠር ትልቅ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። ኢዜአ በባህር ዳር ከተማ በሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ያነጋገራቸው የስራ ዕድል ተጠቃሚ ወጣቶች እንደገለጹት፤ በከተማዋ የኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ወጣቶች በሙያቸው የስራ ዕድል እንዲያገኙ አስችለዋል። በአማራ ብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ኢንተርፕራይዝ የማሽን ባለሙያ የሆነው አባይነህ ታደሰ፤ የተፈጠረለት የስራ ዕድል ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ባሻገር ብቁ የማሽን ባለሙያ እንዲሆን እንዳገዘው ተናግሯል፡፡ በራቫል ስቲል ማኑፋክቸሪንግ የማሽን ባለሙያ የሆነችውና የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተመራቂዋ ፍሬዘር በላይ፤ በተማረችበት ሙያ መሰማራቷ በቂ ተግባራዊ ዕውቀት እንድትቀስም እንዳስቻላት አስታውቃለች። በራቫል ስቲል ማኑፋክቸሪንግ የማሽን ባለሙያው አያሉ መንበረ በበኩሉ፤በቴክኒክ ሙያ ተመርቆ ወደ ሥራ መግባቱንና እያገኘ ያለው የዕውቀት ሽግግር በቀጣይ በዘርፉ የራሱን የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንዳነሳሳው ገልጿል። በንድፈ-ሀሳብ የተማረውን ዕውቀት በተግባር እየሰራበት መሆኑን የጠቀሰው ወጣት እሸቱ አየለ፤ ራቫል ስቲል ፋብሪካ ይበልጥ ውጤታማ ሆኖ ስራውን በማስፋፋት ለሌሎች ወጣቶች የስራ ዕድል እንዲፈጥር ጠንክሮ እንደሚሰራ አረጋግጧል። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ብርሃን ንጉሴ በበኩላቸው በከተማዋ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ በርካታ ባለሀብቶች ወደ ሥራ እየገቡ መሆኑን ገልጸዋል። በከተማዋ በበጀት ዓመቱ አምስት ወራት ብቻ ለስምንት ሺህ ወጣቶች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግረዋል፡፡
ከክልሉ ከ6 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል-ባለስልጣኑ
Dec 26, 2025 56
ዲላ ፤ታህሳስ 17/2018 (ኢዜአ):- ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስካሁን ከ6 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ገለጸ። በክልሉ የቡና ምርት ጥራትና ቁጥጥር ግብር ሃይል በማቋቋም ህገወጥ ንግድና የቡና ብክነትን በመቀነስ የምርት አቅርቦትን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑም ተመላክቷል። የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አማኑኤል ብሩ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ በተያዘው ዓመት ከ131 ሺህ ቶን በላይ ቡና በመሰብሰብ 46 ሺህ 400 ቶን ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው። ለመሰብሰብ ከታቀደውም እስካሁን ከ52 ሺህ ቶን በላይ ቡና መሰብሰብ መቻሉን አቶ አማኑኤል ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥም የላኪ አርሶ አደሮችን አቅም በማጎልበት ከ10 ሺህ ቶን በላይ ልዩ ጣዕም ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ በቅንጅት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል። እስካሁን በተደረገ ጥረትም ከ6 ሺህ ቶን በላይ የታጠበና ጀንፈል ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን ገልፀው በቀጣይ ሶስት ወራትም ከፍተኛ መጠን ያለው ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለመላክ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል። በተለይ የቡና ምርት ጥራትና ቁጥጥር ግብረ-ኃይል በማቋቋም ህገወጥ ንግድና የቡና ብክነትን በመቀነስ የምርት አቅርቦትን ለማሳደግ በተቀናጀ መንገድ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ43 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡም ተመልክቷል።
የመቱ ከተማ የኮሪደር ልማት ገጽታዋን ከመቀየር ባለፈ የስራ እድል ፈጥሯል
Dec 26, 2025 60
መቱ ፤ታኅሣሥ 17/2018 (ኢዜአ)፡- የመቱ ከተማ የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለነዋሪዎች የስራ እድል መፍጠሩን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ ለኢዜአ እንደገለፁት በከተማዋ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ስራ የከተማዋን ገፅታ በመቀየር ለቱሪዝም ተመራጭ ከማድረጉ ባለፈ የስራ ዕድልን ፈጥሮልናል። የኮርደር ልማቱን አስመልክተው ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ የመቱ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ በላይ ተሾመ በከተማዋ የተከናወነው የኮሪደር ልማት የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ ማድረጉን አስረድተዋል። በተለይም በከተማዋ የነበሩ የቆሸሹ አካባቢዎችን በማጽዳት ንጹና ውብ ከተማ በመፍጠር ጤናማ ዜጋን ለማፍራት ማገዙን ጠቁመዋል። የከተማ ኮሪደር ልማት ከተማዋ ለኑሮ ተመራጭ እንድትሆን እያደረጋትና ገጽታዋን መቀየሩን ያነሱት ደግሞ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ታሪኩ ጌታቸው ናቸው። የከተማዋ ልማት ለንግድና ለስራ እድል ፈጠራ ተጨማሪ አቅም መፍጠሩንም አክለዋል። በመጀመሪያ ምዕራፍም ስድስት ኪሎ ሜትር የለማ ሲሆን በሁለተኛው ዙር ደግሞ የመንገድ ልማት፣ የመዝናኛና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራን በማካተት የአምስት ኪሎ ሜትር ልማት መከናወኑን የገለፁት የከተማዋ ምክትል ከንቲባ አቶ ከበደ ነገሱ ናቸው። የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ የተሳለጠ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር ማድረጉንም አክለዋል። በኮርደር ልማቱ የተሰሩት የመዝናኛና የቆሸሹ ስፍራዎችን የማጽዳት ስራ ዜጎች በጤናማ አካባቢ እንዲኖሩ ማድረጉን ጠቁመዋል። የመንገድ ዳር ልማቱን ከመብራትና ውሀ ዝርጋታ ጋር በቅንጅት መሰራቱ ከዚህ ቀደም ይስተዋል የነበረን የመሰረተ ልማት ያለመናበብ ችግርን መቅረፉን አክለዋል። ወጣቶች የእረፍት ጊዜያቸውን ለማሳለፍና ስፖርትን ለማበረታታት የሚያግዙ አነስተኛ የእግር ኳስ ሜዳና መዝናኛ ስፍራዎች በኮሪደር ልማቱ መካተታቸውን ጠቅሰዋል። ይህም የከተማዋ ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ በማድረግ የነዋሪው ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እገዛ እንደሚኖረውም አውስተዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ የተዘጋጀ ነው
Dec 26, 2025 37
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ መዘጋጀቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፥ የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ረቂቅ ፖሊሲን አስመልክቶ ከዲጂታል ካውንስል አባላት ጋር በበይነ መረብ ውይይት አካሂደዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በሁሉም መስክ የሥራ ፈጠራ ባህልን በማስረጽ ቀጣይነት ያለው እና ፈጣን ዕድገትን ዕውን ለማድረግ ኢንተርፕረነርሽፕ ቁልፍ መሳሪያ ነው ብለዋል። ፖሊሲው በዋናነት ሁሉን አቀፍ እና አካታች ሀገራዊ የኢንተርፕረነርሽፕ ንቅናቄን በማቀጣጠል በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ የዲጂታል ሥራ ፈጠራንና ተወዳዳሪነትን የሚያበረታታና የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። የፖሊሲ ማዕቀፉ ችግር ፈች ማህበረሰብን ለመገንባት፣ የፈጠራ ባህልን ለማጎልበት፣ እሴትን ለመጨመር እንዲሁም ምቹ ስነምህዳርን ለመገንባት የሚያስችል የኢኮኖሚ ዕድገት ማዕቀፍ እንደሆነም ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያን የኢንተርፕረነርሽፕ ስነ-ምህዳርና የስራ ፈጠራ ውጥኖችን አቅጣጫ በመስጠት የመምራት ቁልፍ ሚና አለው ነው ያሉት። በተለይ የኢንተርፕረነርሽፕ ስነ-ምህዳሩን ሊያሻሽሉ የሚችሉ የጋራ አመለካከቶችን፣ እምነቶችንንና ባህሪያትን ለማጎልበት በእጅጉ እንደሚያግዝ አብራርተዋል። በውይይቱ የልማት ፖሊሲው የታለመለትን ውጤት ማምጣት እንዲችል በፖሊሲው ትግበራ ወቅት የሚታዩ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖችን በመለየት በየደረጃው ወጥና ጠንካራ የክትትል ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ከዲጂታል ካውንስሉ ጋር መግባባት መፈጠሩን ገልጸዋል። በኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ እና ግብዓቶችን በመጨመር የልማት ፖሊሲ ሰነዱ ወደ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ተልኮ እንዲፀድቅ መወሰኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
የዲላ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ ዲጂታል አገልግሎት ተገልጋዮች ፈጣን መስተንግዶ እንዲያገኙ አስችሏል
Dec 26, 2025 53
ዲላ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦የዲላ ከተማ ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎት ዲጂታል መደረጉን ተከትሎ ፈጣን አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። አገልግሎቱን በማዘመን ከወረቀት ንክኪ ነጻ መደረጉ ለተጠቃሚዎች ፈጣን አገልግሎት ለመስጠትና ገቢን ለማሳደግ ከማስቻሉ ባለፈ የተቋሙን የመፈጸም አቅም ማሳደጉም ተመላክቷል። የከተማው ነዋሪዎች ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ዲጂታል መደረጉን ተከትሎ ፈጣንና የተሻለ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን አንስተዋል። ከዚህ ቀደም በማዘጋጃ ቤቱ አንድ ጉዳይ ለማስጨረስ በቀጠሮ የሚያጠፉት ጊዜና ጉልበትን ከማስቀረቱ ባለፈ ለብልሹ አሰራር የነበረባቸውን ተጋላጭነትም በእጅጉ መቀነሱን ተናግረዋል። ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎች መካከል አቶ ከበደ ወራሳ፤ በወረቀት ያለውን የካዳስተር ይዞታቸውን ወደ ዲጂታል ለመቀየር እንደመጡ ገልጸው፣ በአንድ ቀን ጉዳያቸውን ጨርሰው በመመለሳቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል። ይህም ከዚህ ቀደም አንድ ጉዳይ ለማስጨረስ ለበርካታ ቀናት ሲደርስባቸው የነበረውን እንግልትና ምልልስ በማስቀረት የጊዜና የገንዝብ ብክነትን እንዳስቀረላቸው አንስተዋል። በመንደራቸው ከረጅም ጊዜ በፊት ተለክቶ ያልተሰራ መንገድ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ ጫና በመፍጠሩ ይህን የህዝብ ቅሬታ ይዘው እንደመጡ የገለጹት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ክፍሌ ሎላ ናቸው። በማዘጋጃ ቤቱ በተጀመረው የፊት ለፊት አገልግሎት የልማት ጥያቄያቸው ለሚመለከተው የሥራ ሃላፊ ቀርቦ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። በማዘጋጃ ቤቱ የተጀመረው ዘመናዊ አገልግሎት ከዚህ ቀደም አንድ ጉዳይ ለማስጨረስ ከቢሮ ቢሮ የቀጠሮ ምልልስ ነበረው፤ በዚህም ጊዜና ጉልበት ይባክን ነበር ብለዋል። ማዘጋጃ ቤቱ አገልግሎቱን ማዘመኑ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማስቻሉ ባለፈ ለብልሹ አሰራር የነበራቸውን ተጋላጭነት በእጅጉ መቀነሱን አስረድተዋል። የመኖሪያ ቤት ጥያቄያቸውን ይዘው ለረጅም ጊዜ ምላሽ ሳያገኙ ተቸግረው መቆየታቸውን የተናገሩት ወይዘሮ ሃያሌ ሠራዊት የተባሉ ነዋሪ በበኩላቸው፣ ማዘጋጃ ቤቱ አገልግሎቱን ማዘመኑን ተከትሎ ጥያቄያቸው ሰሚ አግኝቶ በሚመለከተው የሥራ ክፍል እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። ዲጂታል አገልግሎቱ በማዘጋጃ ቤቱ ከዚህ በፊት የሚነሳውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግር የቀረፈ ነው ብለዋል። ተቋሙ ከተያዘው በጀት ዓመት ጀምሮ አሰራሩን በማዘመን የግንባታ፣ መሬት አስተዳደር፣ የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢን ጨምሮ 71 አገልግሎቶችን ዲጂታል ማድረጉን ያነሱት ደግሞ የዲላ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሃብታሙ ተፈሪ ናቸው። በዚህም አገልግሎቶች ከወረቀት ንክኪ ነጻ በሆነ መንገድ እየተሰጡ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ይህም ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን ማህበረሰብ ጊዜና ጉልበት ለመቆጠብ ማስቻሉን ጠቁመዋል። በቴክኖሎጂ ታግዞ የሚሰራው ሥራ የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ከመፍታት ባለፈ የተቋሙን የእለት ገቢና የመፈጸም አቅም አሳድጎታል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር በተጓዳኝ ለዲጂታል ልማት ስኬት የበኩሉን እየተወጣ ነው
Dec 26, 2025 59
ጂንካ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ስራው በተጓዳኝ ለዲጂታል ልማት ስኬት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ገለጸ። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከእውቀት ማእከልነቱ ባለፈ ለባህልና ለተፈጥሮ ሃብት ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት አካባቢያዊ እውቀትን ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት ለማህበረሰብ እመርታዊ ለውጥና ተጠቃሚነት እየሰራ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው በተለይም በማህበረሰብ ተኮር ምርምሮች እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዙሪያ ትኩረት አድርጎ ከሚሰራባቸው ዋና ዋና ዘርፎች መካከል በግብርና እና የእንስሳት ሃብት፣ የቱሪዝም ልማትና የባህል ጥበቃ፣ የማህበረሰብ አገልግሎት የፈጠራ ስራዎች፣ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና ሌሎችም ይገኙበታል። በመሆኑም በዚህ ሰፊ የስራ እንቅስቃሴ ውስጥ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራትንና የቀጣይ አቅጣጫዎች በተመለከተ ኢዜአ በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን ካሳሁን የማነህ (ዶ/ር) አነጋግሯል። የዲጂታል ኢትዮጵያን እቅድ በማሳካት ሂደት የ5 ሚሊዮን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና አንዱ መሆኑን አንስተው በዚህ ጥረት ውስጥ ዩኒቨርሲቲው የድርሻውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል። የኮደርስ ስልጠና ከወሰዱት የዩኒቨርሲቲው መምህራን፣ ተማሪዎችና ሰራተኞች መካከል 1 ሺህ 73ቱ ሰርተፍኬት መውሰዳቸውን ገልጸዋል። አሁን ላይ በዩኒቨርሲቲው የኤሌክትሮኒክ ትምህርት ክፍል አስተባባሪነት 1 ሺህ 879 የሚሆኑ መምህራን፣ተማሪዎችና የአስተዳደር ሰራተኞች የኮደርስ ስልጠና እየተከታተሉ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በማስፋትና በማበልፀግ በዘርፉ የካበተ ዕውቀት ያለው ዜጋ ለማፍራት የበኩሉን ይወጣል ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የኮደርስ ስልጠና ከወሰዱት መካከል መምህር አስመራ አምዴ፤ የኮደርስ ስልጠና ዘመኑ የሚጠይቀው የዲጂታል ቴክኖሎጂ እውቀት መሆኑን ገልጸው እድሉን በአግባቡ መጠቀም ይገባል ብለዋል። በዚህ ዘመን የሰው ሰራሽ አስተውሎትና ሌሎችም ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተግባርና የፈጠራ አቅምን ማሳደግ አስፈላጊ ስለመሆኑም አንስተዋል። በዩኒቨርሲቲው የአይ ሲቲ ጥገና ባለሙያ ግዛቸው ገንዶሌ፤ የኮደርስ ስልጠና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪና ብቁ ባለሙያ ሆኖ ለመገኘት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮ ኮደርስ ከተዘጋጁ 4 ኮርሶች 3ቱን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ገልፀው፥በቀጣይም ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ማቀዳቸውንም ተናግረዋል ። ኮርሱ የያዛቸው ይዘቶች እጅግ ጠቃሚና የዲጂታል ክህሎትን የሚያሰፋ በመሆኑ ሌሎችም የነፃ ስልጠና እድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መክረዋል።
በዲጂታል ልማት ዘርፍ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በአገልግሎት አሰጣጥና በሰዎች የኑሮ ዘይቤ ላይ እመርታዊ ለውጥ አምጥቷል - ምሁራን
Dec 26, 2025 54
ሐረማያ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦ በዲጂታል ልማት ዘርፍ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በአገልግሎት አሰጣጥና በሰዎች የኑሮ ዘይቤ ላይ እመርታዊ ለውጥ ማምጣቱን በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ላለፉት አምስት ዓመታት ሲተገበር ቆይቶ በቅርቡ በስኬት መጠናቀቁ ይታወቃል። በዚህ የትግበራ ሂደት በቴሌኮም እና ኢንተርኔት መሠረተ ልማት፤ በዲጂታል ክፍያ እና የፋይናንስ ዘርፍ፤ በዲጂታል መታወቂያ እና በተለያዩ የመንግስት አገልግሎቶች ላይ የሚታዩ ለውጦችና ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በመሆኑም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በይፋ ተጀምሯል። ከዲጂታል ልማት ትግበራ እና የቀጣዩን እቅድ በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን በዲጂታል ልማት ዘርፍ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በአገልግሎት አሰጣጥና በሰዎች የኑሮ ዘይቤ ላይ እመርታዊ ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል ሃላፊና መምህር ሚልኬሳ ደጀኔ፤ በዲጂታል ዘርፍ ኢትዮጵያ እመርታዊ ለውጥና ማንሰራራት ላይ መሆኗን ብዙ ማሳያዎች እንዳሉ ተናግረዋል። በቴሌኮም እና የኢንተርኔት መሠረተ ልማት፣ በፋይናንስ፣ በተለያዩ የመንግስት አገልግሎቶችና ሌሎችም በዲጂታል አገልግሎት የሚገለጡ ማሳያዎች አሉ ብለዋል። ከዚህ ስኬት በመነሳትም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ቁልፍ ትልሞች ስኬታማ እንደሚሆኑ ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው የኮምፒቲንግና ኢንፎርማቲክ ኮሌጅ ምክትል ዲንና መምህር አፈንዲ አብዲ፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በኢትዮ ቴሌኮም መሰረተ ልማት ማስፋፋት ጋር በተያያዘ የ4ጂ እና 5ጂ ኔትወርክ ዝርጋታ ለዘርፉ ልማት ፅኑ መሰረት ማኖሩን ገልጸዋል። ከዚህ በመነሳት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ተደራሽነትን የማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እና በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመንን የመፍጠር ቁልፍ ተግባር በቀላሉ የሚሳካ መሆኑን አንስተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ ይፋ የተደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ያለፈውን ስኬት በማስቀጠል በዘርፉ ልማት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚያስችል ነው።
ስፖርት
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድን ጋር አቻ ተለያየ
Dec 26, 2025 32
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት ሲዳማ ቡና እና ኢትዮጵያ መድን ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቋል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ረመዳን በ18ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ መድን መሪ ሆኗል። ብርሃኑ በቀለ በ29ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ጎል ሲዳማ ቡናን አቻ አድርጋለች። የሲዳማ ቡናው አጥቂ ሀብታሙ ታደሰ ከእረፍት መልስ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። ውጤቱን ተከትሎ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ነጥቡን ወደ 22 ከፍ አድርጓል። ከተከታዩ ፋሲል ከነማ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ለማስፋት ያገኘውን እድል አልተጠቀመም። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በ13 ነጥብ ደረጃውን ከ16ኛ ወደ 13ኛ ከፍ አድርጓል። ዛሬ በተደረገው ሌላኛው ጨዋታ መቻል አዳማ ከተማን 3 ለ 1 አሸንፏል። መቻል ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል ጨዋታዎቹን ተከትሎ የ11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የ12ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ እንደሚካሄዱ የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል።
አንጎላ እና ዚምባቡዌ ነጥብ ተጋሩ
Dec 26, 2025 30
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት ጨዋታ አንጎላ እና ዚምባቡዌ አንድ አቻ ተለያይተዋል። በማራካሽ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጌልሰን ዳላ በ24ኛው ደቂቃ አንጎላን መሪ ያደረገችውን ጎል አስቆጥሯል። የመጀመሪያ አጋማሽ የባከኑ ደቂቃዎች ላይ ኖውሌጅ ሙሶና ከመረብ ላይ ያሳረፋት ግብ ዚምባቡዌን አቻ አድርጓል። ለግቧ መቆጠር የአንጎላ ተከላካዮች ድክመት ትልቅ ድርሻ ይወስዳል። ጨዋታው አዝናኝ እና ጠንካራ ፉክክር ተደርጎበታል። ውጤቱን ተከትሎ አንጎላ እና ዚምባቡዌ በምድብ ሁለት የመጀመሪያ ነጥባቸውን አግኝተዋል። በዚሁ ምድብ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ግብጽ ከደቡብ አፍሪካ በማራካሽ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
መቻል ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል
Dec 26, 2025 39
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር መቻል አዳማ ከተማን 3 ለ 1 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ መሐመድ አበራ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር በረከት ደስታ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ተቀይሮ የገባው አህመድ ሁሴን ለአዳማ ከተማ ብቸኛውን ግብ አስቆጥሯል። ከስድስት የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል የተመለሰው መቻል በ18 ነጥብ ደረጃውን ከዘጠነኛ ወደ አምስተኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ያሸነፋቸውን ጨዋታዎች ብዛትም አራት አድርሷል። በአንጻሩ በሊጉ ሁለተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አዳማ ከተማ በ17 ነጥብ ከነበረበት አምስተኛ ደረጃ ወደ ሰባተኛ ዝቅ ብሏል።
በፕሪሚየር ሊጉ የ”ቦክሲንግ ደይ” መርሃ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከኒውካስትል ዩናይትድ ጋር ይጫወታል
Dec 26, 2025 84
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ):- የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት የመጀመሪያ መርሃ ግብር በማንችስተር ዩናይትድ እና ኒውካስትል ዩናይትድ መካከል ዛሬ ይካሄዳል። ጨዋታው ምሽት አምስት ሰዓት በኦልድትራፎርድ ስታዲየም ይደረጋል። ማንችስተር ዩናይትድ በ26 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ኒውካስትል ዩናይትድ ደግሞ በ23 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 60 የርስ በርስ ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ 33 ጊዜ ሲያሸንፍ ኒውካስትል ዩናይትድ 11 ጊዜ ድል ቀንቶት 16 ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥተዋል። ማንችስተር ዩናይትድ በጨዋታዎቹ 117 ግቦችን ሲያስቆጥር ቦርንማውዝ 68 ጎሎችን ከመረብ አሳርፏል። ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች በነበራቸው የእርስ በእርስ ግንኙነት ኒውካስትል ዩናይትድ አራት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ አቻ ወጥተዋል። ወጥ ብቃት ማሳየት የተሳነው ማንችስተር ዩናይትድ ሶስት ነጥብ ማግኘት ወደ አሸናፊነት እንዲመለስ ያደርገዋል። ኒውካስትል ዩናይትድ ከሁለት የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። የ47 ዓመቱ እንግሊዛዊ አንቶኒ ቴይለር ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ይመሩታል። ‘ቦክሲንግ ዴይ’ የፈረንጆች ገና በተከበረ በቀጣዩ ቀን ያለው ስያሜ ሲሆን በገና ወቅት በርካቶች ስጦታ የሚሰጣጡት በሳጥን(Box) መሆኑን ተከትሎ በዛን ወቅት የሚደረጉ ጨዋታዎችም ቦክሲንግ ዴይ ተብለው ተሰይመዋል። ‘ቦክሲንግ ዴይ’ በዩናይትድ ኪንግደም የሚኖሩ ዜጎች የበጎ አድራጎት እና መልካም ተግባር የሚከውኑበት ዕለት ነው። ክለቦች በቦክሲንግ ዴይ ጨዋታዎች የትኬት ዋጋ ላይ ከፍተኛ ቅናሽ በማድረግ በተለይ ሕጻናት ስታዲየም እንዲገቡ ያበረታታሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራው ምርታማነትን ጨምሮልናል- አርሶ አደሮች
Dec 26, 2025 79
ሰቆጣ፤ ታኅሣስ 17/2018 (ኢዜአ)፡- ቀደም ሲል የሠራነው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ የሰብልና የእንስሳት መኖ ምርታማነትን ጨምሮልናል ሲሉ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር የፃግብጅ ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ። የአሥተዳደሩ የ2018 ዓ.ም የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ በፃግብጅ ወረዳ 01 ቀበሌ ማላባ ተፋሰስ ዛሬ ተጀምሯል። በዚሁ ወቅት አርሶ አደር ግርማይ ብዙ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በየዓመቱ ሲያከናውኑት የቆየው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። አካባቢያችን ዝናብ አጠር በመሆኑ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራን በልዩ ትኩረት አጠናክረን ቀጥለናል ብለዋል። የሠራናቸው እርከኖች የአፈር ለምነትና እርጥበት የመያዝ ዐቅም እንዲጨምር በማድረግ ምርታማነታችን እንዲያድግ አስችለዋል ሲሉም ገልጸዋል። የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራን በማጠናከራቸው የተጎዳው መሬታቸው ማጋገሙን ብሎም ከጎርፍ ስጋት ነጻ መሆኑንና የእንስሳት መኖ ምርታማነትም መጨመሩን የገለጹት ደግሞ አርሶ አደር ግርማይ ጌታሁን ናቸው። በዚህም መሠረት እየተገኙ ያሉ ጥቅሞችን አስፋፍቶ ለማስቀጠል በዘንድሮው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ በንቃት መሣተፍ መጀመራቸውን ተናግረዋል። አርሶ አደር ደሳለኝ መኮንን በበኩላቸው፤ ጠፍተው የነበሩ ምንጮች በተከናወኑ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራዎች ምክንያት ጎልብተው ለመስኖ ልማት መዋላቸውን እና በዚህም ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። በሌላ በኩል ዘንድሮ በ366 ተፋሰሶች የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ሥራ እንደሚከናወን የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ግብርና መምሪያ ኃላፊ አዲስ ወልዴ ጠቁመዋል። የተፋሰሶች ኅብረት ሥራ ማኅበራት በማቋቋም ሕብረተሰቡም እንዲጠብቅና እንዲንከባከብ በማድረግ ዘላቂ ተጠቃሚነቱን እንዲያረጋግጥ እየተሠራ ነው ብለዋል። የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ሥራ ዝናብ አጠር ለሆኑ ለአካባቢዎች ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ባለፉት ዓመታት የለሙ ተፋሰሶች ምርታማነትን ከማሳደግ በተጨማሪ ለንብ ማነብ ሥራ ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውንም አስረድተዋል። ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋጋጥ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራን በይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ የተናገሩት ደግሞ የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ምክትል አሥተዳዳሪ፣ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ሹመት ጥላሁን ናቸው። በአሥተዳደሩ በዘንድሮው በጋ ከ138 ሺህ በላይ ሰዎችን በማሳተፍ በሚካሄደው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ሥራ ከ2 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት እንደሚሸፈን ተገልጿል።
የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ አርሶ አደሮች ምርታማነታቸው እንዲያድግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Dec 24, 2025 142
ባሕርዳር ፤ ታህሳስ 15/2018 (ኢዜአ)፡ - ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የተጎዳው መሬታቸው አገግሞ ምርታማነታቸው እንዲያድግ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው በባሕርዳር አስተዳደር የዘንዘልማ ቀበሌ አርሶ አደሮች ተናገሩ። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ዛሬ በዘንዘልማ ቀበሌ በንቅናቄ አስጀምሯል። በማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል። ከተሳታፊ አርሶ አደሮች ውስጥ የዘንዘልማ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ሙላት መኮንን ፤ ለዓመታት ያከናወንነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የልፋታችንን ዋጋ መልሶ እየከፈለን ነው ሲሉ ለኢዜአ ገልጸዋል። በዚህም ሰብልን ማብቀል ወደ ማቆም ተቃርቦ የነበረው መሬታቸው ለምነቱ እንዲጨምር በማድረጉ የሰብል ምርታማነታቸው እንዲያድግ ብሎም በቂ የእንስሳት መኖ እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው ተናግረዋል። በተጨማሪም በማሳቸው አካባቢ የተከሏቸው የማንጎና ሌሎች የፍራፍሬ ተክሎች ለውጤት በቅተው ተጠቃሚ እንደሆኑ አንስተው፤ዛሬ በተጀመረው ስራ ያለምንም ቀስቃሽ በንቃት መሳተፋቸውንና እንደሚቀጥሉበትም ገልጸዋል። አርሶ አደር ደስታው ማንዴ በበኩላቸው፤ ተጠቃሚነታችንን እያረጋገጠልን ያለው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ በመጀመሩ ተደስቼያለሁ ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወነው ስራ ምርታማነታቸው ማደጉን ገልጸው፤ ያገኘሁትን ጥቅም ለማሳደግም ዛሬ በተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ያለማንም ቀስቃሽ ወጥተን እየሰራን ነው ሲሉ ገልጸዋል። በባሕር ዳር ከተማ ዛሬ በተጀመረው የተፋሰስ ልማት ስራ በጥራትና በውጤታማነት ተምሳሌት እንዲሆን አስፈላጊው እገዛ እንደሚደረግ የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ መሰሉ ብርሃኑ ናቸው። ባለፉት ዓመታት የተራቆቱ አካባቢዎችን በመለየት የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ በመሰራቱና ከእንስሳት ንክኪ ነጻ በመደረጉ የአየር ንብረቱ እንዲስተካከልና የዝናብ መጠኑ እየጨመረ እንዲመጣ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። በሚለሙ ተፋሰሶች ላይ አርሶ አደሩ የፍራፍሬና የመኖ ችግኞችን እንዲተክል በማድረግ ዘላቂ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱን እንዲያረጋግጥ የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ፤ የዘንድሮው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ስራ በአስተዳደሩ ስር በሚገኙ በ12 የገጠር ቀበሌዎች በጥራት እንደሚካሄድ ገልጸዋል። በተለዩ ተፋሰሶች ከ1ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለማከናወን ዛሬ የተጀመረው ተግባር በቀጣይ ለ30 ቀናት እንደሚቆይ ተናግረዋል።
በመገጭ ግድብ አዋሳኝ በሆኑ ተፋሰሶች የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ማከናወን ተጀመረ
Dec 24, 2025 174
ጎንደር፣ ታኅሣስ 15/2018 (ኢዜአ)፡- የመገጭ የመስኖና የመጠጥ ውኃ ግድብን ከደለል ለመጠበቅ የሚያስችል ሕብረተሰቡን ያሳተፈ የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ዛሬ ተጀምሯል። የዘንድሮው የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት በጎንደር ከተማ አሥተዳደር ድባ ደፈጫ ቀበሌ ተካሂዷል፡፡ በዚሁ ወቅት የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው እንዳሉት፤ የዘንድሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ የመገጭ ግድብ አዋሳኝ በሆኑ 18 ተፋሰሶች ላይ ይካሄዳል። በዚህም መሠረት የማሳ እርከንና ክትር ሥራ እንደሚሠራና ሀገር በቀል ችግኞችም እንደሚተከሉ ጠቁመዋል። የጎንደር ከተማን ሕዝብ የረጅም ዓመታት የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ጥያቄ በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ እየተገነባ ያለውን ግድብ በደለል እንዳይሞላ ከወዲሁ መጠበቅ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ አርሶ አደሮች ምርታማነታቸው እንዲያድግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል በክልሉ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ ለማጠናከር ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል በዞኑ በአንድ ሺህ 52 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው በአሥተዳደሩ ሥር በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች 847 ሔክታር የሚሸፍን የእርከንና ክትር ሥራ በግድቡ ተፋሰሶች ይከናወናል ያሉት ደግሞ የከተማ አሥተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አበራ አደባ ናቸው፡፡ ለአንድ ወር በሚቆየው የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ከ8 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል። ቀደም ሲል በሕብረተሰቡ ተሳትፎ የተከናወኑ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራዎች የአፈር ለምነትን በመጨመር የሰብል ምርታማነት እንዲያድግ ማስቻላቸውንም አንስተዋል። በለሙ ተፋሰሶች በእንስሳት ማድለብ፣ በንብ ማነብ፣ በወተት ሀብትና በፍራፍሬ ልማት ዘርፍ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እየጨመረ መምጣቱንም አመላክተዋል። በሥራው የተሳተፉ አርሶ አደሮች በበኩላቸው፤ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ በአነስተኛ መሬት ብዙ ምርት እንድናገኝና ለእንስሳት በቂ የመኖ እንድናቀርብ አስችሎናል ብለዋል፡፡ የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ምንጮች ጎልብተው መስኖ እንዲጠቀሙ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸውም ጠቅሰዋል።
በክልሉ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ ለማጠናከር ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል
Dec 24, 2025 115
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁሉም ሰው የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተመላከተ። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ በዘንዘልማ ቀበሌ ዛሬ ተጀምሯል። በመርሃ ግብሩ የተገኙት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ መሰሉ ብርሃኑ እንዳሉት፤ የተጎዳ አካባቢን ወደ ነበረበት ለመመለስ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ማጠናከር ያስፈልጋል። ከተያዘው ወር መግቢያ ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በተለዩ ተፋሰሶች የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ዘንዘልማ ቀበሌ የተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ጣናን ከደለል የሚታደግ እንደሆነም ገልጸዋል። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የተጀመረው የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁሉም ሰው የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባም አመልክተዋል። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ ከዛሬ ጀምሮ ለ30 ቀናት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራው በ12 ቀበሌዎች በተለዩ 24 ተፋሰሶች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራው ጥራቱን በጠበቀና ዘላቂነት ባለው መልኩ በማከናወን ወደ ጣና ኃይቅ የሚገባውን ደለል መከላከል በሚያስችል አግባብ እንዲከናወን ክትትል እንደሚደረግ ተናግረዋል። በዘንዘልማ ቀበሌ በተጀመረው የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ መርሃ ግብር የክልልና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎችና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት፤ የአፍሪካ ህብረት የ2026 መሪ ሀሳብ ዋና የትኩረት አጀንዳ
Dec 26, 2025 114
39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ነው። መሪ ሀሳቡን ያረቀቀው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የዘንድሮው መሪ ቃል ከአጀንዳ 2063 ጋር የተቆራኘ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። ሁሉም አፍሪካዊ ንጹህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በቂ ውሃ ለመጠጥ፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና ለሌሎች ፍላጎቶቹ እንዲያገኝ የማድረግ ራዕይን ለማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል። ህብረቱ የውሃ ደህንነት እንደ አህጉር የተያዙ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን በማዕቀፎቹ አስቀምጧል። ውሃ እና ንጽህና የኢኮኖሚ እድሎችን በማስፋት፣ የስራ አጥነት ምጣኔን በመቀነስ፣ የስደቶችና ተፈናቃዮችን ጫና ለማቃለል እንዲሁም ለሰላምና ደህንነት መስፈን አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተመላክቷል። የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ህብረቱ ውሃ እና ንጽህና ለጤና፣ ለኢኮኖሚ እድገት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥና ዘላቂ የአካባቢ ምህዳር ለመፍጠር መሰረት መሆኑን የበለጠ እውቅና እንደተሰጠው አመልክቷል። ሁሉን አቀፍ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይገበር የውሃ ደህንነትን የማረጋገጥ አላማ ካለው የአፍሪካ የውሃ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው። የዘንድሮው መሪ ቃል የአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ጥረቶችን ያስተሳሰረ ድልድይ ሆኗል። በዘላቂ ልማት ግቦች ውስጥ ያለው ግብ ስድስት ከውሃ እና ንጽህና ጋር የተያያዘ ነው። ይህ ግብ እ.አ.አ በ2030 ለሁሌም ዜጋ ደህንነቱ የተረጋገጠ ውሃ አቅርቦትና የንጽህና አጠባበቅን ተደራሽ የማድረግ አላማ አለው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት በፍጥነት መስፋፋትና ውሃ በአግባቡ አለመጠቀም የውሃ ደህንነት እና ዘላቂ አቅርቦት ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። የንጽህና አጠባበቅ የአፍሪካ አንዱ ፈተና ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች መሰረታዊ የሚባል የንጽህና መጠበቂያ መሰረተ ልማቶችን አያገኙም። ይህም እንደ ኮሌራ ላሉ የውሃ ወለድ በሽታዎች መስፋፋት ምክንያት ሆኗል። የተቀናጀ የውሃ አስተዳደር ስርዓት፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ ለዘላቂ መሰረተ ልማት የሚፈሰወን መዋዕለ ንዋይን ማሳደግ፣ ውሃ በድጋሚ አጣርቶ መጠቀም፣ የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ፣ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር እና ለውሃ ደህንነት ትኩረት የሚሰጡ ፖሊሲዎችና ማዕቀፎችን በውጤታማነት መተግበር ያሉትን እድሎች በዘላቂነት ለመፍታትና ፈተናዎችን ለመቅረፍ ያስችላል። ደህንነቱ የተረጋገጠ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ላይ ያለፈውን ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የቆሸሸ ውሃ በአግባቡ ማከም፣ የንጽህና አጠባበቅ ማስፋትና የግንዛቤ ፈጠራ ስራን በስፋት ማከናወን፣ ማህበረሰብ መር የንጽህና አጠባበቅ ኢኒሼቲቮችን ትግበራ ማስፋት፣ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎችና ሀገር በቀል አቅምን መገንባት ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓትን መፍጠር ያስችላል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና ጤናማ ማህበረሰብ ግንባታ ያላቸውን ቁልፍ ሚና የሚያሳይ ነው። የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ማድረግ መሰረታዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ ለማህበረሰብ ደህንነትና የተሻለ የኑሮ ዘይቤ፣ ለአካባቢ ጥበቃና ለአፍሪካ ብልጽግና መረጋገጥ ስትራቴካዊ አቅም ናቸው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በሚካሄድበት ወቅት በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም እና 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኞች ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳሉ። ኢትዮጵያ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የአፍሪካ ጣሊያን ስብሰባን ለማዘጋጀት ብሄራዊ የዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቀን ነው - የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Dec 24, 2025 195
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ሲል የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ገለጸ። የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በኤርትራ መንግሥት አገዛዝ ደረሰብን ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ጋምቢያ(ባንጁል) የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ላቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን አድንቋል። በኤርትራ መንግስት ላይ የቀረቡትን ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክስ ተቀብሎ በመዝገብ ቁጥር 868/25 መመዝገቡን፣ የክሱ ፍሬ ነገር እና ይዘት ተቀባይነት ያለው መሆኑን እውቅና በመስጠት የኤርትራ መንግስት እንዲመልስ ክሱን መላኩን ኮሚሽኑ ማስታወቁን ገልጿል። የድርጅቱ ሊቀ-መንበር ኢብራሂም ሀሩን በመግለጫቸው እንደተናገሩት፤ የኤርትራው መንግሥት በደናክል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ህዝቦች እየፈፀመ ያለው መጠነ ሰፊ፣ ስልታዊ፣ መንግስታዊ መር እና ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በአሁኑ ወቅት እየደረሱ ነው ካሏቸው የመብት ጥሰቶች መካከልም ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ማካሄድ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት፣ በሺዎች የሚቆጠሩትን መሰወር፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ማከናወን መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰው፤ በተለይም ከ300ሺህ በላይ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማፈናቀል እና ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል፣ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋትና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን መጣስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ድርጅቱ የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ከ1993 ጀምሮ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰባቸው ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ክስ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እኤአ ጁን 04 ቀን 2025 በ122 ገጽ የተደራጀ ክስ ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የኤርትራ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን እንደገለጸላቸው ጠቁመዋል። ለክሱም ከተጠቀሙት ማስረጃዎች መካከል በድርጅቱ የተከናወነ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ግኝት፣ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝባዊ መብቶች በኤርትራ ላይ የተደረጉ ምርመራዎች፣ ግኝቶችና ማስረጃዎች፣ የመብት ጥሰት የደረሰባቸው የቀይ ባሕር አፋር ተጎጂ ወገኖች እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የተገኙ የሰብዓዊ መብት ምርመራዎችን መቅረቡን ተናግረዋል። ድርጅቱ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት መከራ ለማዳን፣ የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ድምፅ እንዲሆኑት፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡንና የኢሳያስ መንግስት ላይ ህጋዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጸንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው-ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
Dec 23, 2025 166
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እና ለረጅም ጊዜ ፀንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ኃላፊ አምባሳደር ኮንስታንሲያ አዴሊና ጋስፓራስ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቅርበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት (ዋይት ሃውስ) በተካሄደ ስነ ስርዓት የአምባሳደር ኮንስታንሲያን ሹመት በይፋ ተቀብለዋል። አምባሳደሯ በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ቢሮ ስራቸውን በይፋ ጀምረዋል። ዶናልድ ትራምፕ የአምባሳደር ኮንስታንሲያ የልዑኩ መሪ ሆኖ መመረጥ በጋራ የኢኮኖሚ እድሎች፣ በሉዓላዊ አመራር ሰጪነት እንዲሁም በሰላም እና ደህንነት ላይ የተመሰረተውን የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጽኑ አጋርነት የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በአፍሪካ ሰላም፣ ብልጽግና እና መረጋጋትን ማረጋገጥን ዋና ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የአጋርነት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኝ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት የማጠናከር ፍላጎት አላት -ተሰናባቹ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና
Dec 20, 2025 226
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ሽብርተኝነትን መዋጋትን ጨምሮ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት ለማጎልበት በጋራ መስራቷን እንደምትቀጥል ተሰናባቹ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና ገለጹ። አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ ትብብር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ያለው መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ሀገራቱ የኬንያው የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና መስራች አባት ጆሞ ኬንያታ እና ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ጊዜ አንስቶ ወዳጅነት እንደነበራቸው አውስተው ትብብሩ በከፍተኛ ደረጃ በሚደረጉ ጉብኝቶች እና ውይይቶች እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ጠንካራ አጋርነት ፈጥረው እየሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ጨምሮ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመዋጋት እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ሰላም እና ደህንነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ እና የኬንያ የንግድ ትብብር እያደገ መምጣቱን የገለጹት ተሰናባቹ አምባሳደር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብሩን አድማስ የበለጠ እንደሚያሰፋው ነው የተናገሩት። ቱሪዝም እና ንግድ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ ትስስር እንዲጎለብት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ፣ ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው የ"ላፕሴት ፕሮጀክት" እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ጨምሮ በሌሎች መሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ትስስሩን የሚያሳልጡ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባሳደር ጆርጅ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በማስመረቋ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ግድቡ በቀጣናው ሽግግርን የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1963 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ቀጣናዊ መረጋጋት እና ደህንነት ፣ ንግድ እና የመሰረት ልማት ትስስር የሀገራቱ ዋንጫ የትብብር መስኮች ናቸው።
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 358
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 549
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 872
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል። የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 1071
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 715
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3135
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 3067
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3968
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 2573
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1653
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7467
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5955
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ እና የህንድ ዘመን አይሽሬ እና ድንበር ተሻጋሪ ወዳጅነት
Dec 16, 2025 470
በሙሴ መለስ (ኢዜአ) ኢትዮጵያ እና ህንድ ረጅም ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አላቸው። በዚህም የስልጣኔ እሴቶችን ይጋራሉ። ሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከፈጠሩ ከ2000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እና ህንድ ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳሽነት እንደሆነም ይወሳል። ኢትዮጵያ እና ህንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1948 ነው። እ.አ.አ በ1950 ሳርዳት ሳንት ሲንግ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያ እና ህንድ በየሀገራቱ ኤምባሲ በመክፈት የዲፕሎማሲ ትብብሩን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ገልጸዋል። ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ እ.አ.አ በ1956 እና በ1958 በህንድ ያደረጓቸው ጉብኝቶች ከኢትዮጵያ መሪዎች ጉብኝቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። እ.አ.አ 1960 ዎቹ ማብቂያ እና 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የህንድ ፕሬዝዳንቶች የነበሩት ሳርቬፓሊ ራድሃክሪሽናን እና ዛኪር ሁሴን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝቶችን አድርገዋል። እ.አ.አ በ2011 ከአንድ ዓመት በፊት ህይታቸው ያለፈው የቀድሞው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንሞሃን ሲንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝትም ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው የህንድ ፕሬዝዳንት ራም ናት ኮቪንድ እ.አ.አ በ2017 የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ በጉብኝታቸው ህንድ እና ኢትዮጵያ በንግድ፣ ኮሙኒኬሽን እና የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 15ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የሀገራቱ መሪዎች በወቅቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ የወጣቶች ክህሎት ማጎልበት እና በሕዝብ ለሕዝብ ልውውጥ ዙሪያ ትብብርን በማጠናከር ዙሪያ ተወያይተዋል። በወቅቱ ህንድ ባዘጋጀችው የሁለተኛው “Voice of Global South Summit” በተሰኘው ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተሳትፎ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲ በህንድ አጠቃላይ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈውም ነበር። የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን የደስታ መግለጫ መልዕክት በመቀበል በአዲሱ የስልጣን ዘመናቸው ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት አጋርነት እንደሚያድግ መግለጻቸውም ይታወሳል። ህንድ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላቸውን አጋርነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። በዚህም ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ትብብር ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥም ነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ያስታወቁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 20ኛው የቡድን 20 አባላት ሀገራት ጉባኤ ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ትርጉም ያለው እና ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ህንድ የቡድን 20 አባል ሀገር መሆኗ የሀገራቱን የባለብዙ ወገን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር ነው። ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ሀገራቱ የሁለትዮሽ እና የባለዙወገን ትብብራቸውን የሚያጠናክሩ ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በወቅቱ የህንድ የትምህርት፣ ንግድ፣ ልማት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የሀገራቱ ግንኙነት የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ድጋፍ ያደረገች ሲሆን በብዝሃ ወገን ማዕቀፉ ሁለቱ ሀገራት በትብብር እየሰሩም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ህንድ በተለያዩ ጊዜያት በአየር ትራንስፖርት፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ መከላከያ፣ ተደራራቢ ታክስን የማስቀረት፣ ንግድ፣ ኮሙኒኬሽን ሳይንስ፣ባህል፣ ትምህርት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መስራት የሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 2025 ኢትዮጵያ እና ህንድ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ የተፈራረሙት የሁለትዮሽ ስምምነት ቁልፍ የሚባል ነው። እ.አ.አ በ2023/24 በወጣ መረጃ የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ምጣኔ 271 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ኢትዮጵያ አተር፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቆዳ ውጤቶች እና የከበሩ ድንጋዮችን ወደ ህንድ ትልካለች። ከህንድ ደግሞ ማሽነሪዎች፣ የመድኃኒትት ምርቶች እና የብረታ ብረት ውጤቶችን በዋናነት ታስገባለች። ህንድ የኢትዮጵያ ዋንኛ የኢንቨስትመንት አጋር ከሚባሉ ሀገራት መካከል ትጠቀሳለች። ከ500 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በጨርቃ ጨርቅ፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ። ህንድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ታደርጋለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ጤና እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከሁለቱ ሀገራት አበይት የትብብር መስኮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ የጉብኝታቸው መርሃ ግብር ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶች እና የጉብኝት ልውውጦች የኢትዮጵያ እና የህንድን ግንኙነት የበለጠ የሚያጸኑ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ህንድ በታዳሽ ኃይል፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ግብርና ማቀነባበሪያን ጨምሮ በአዳዲስ መስኮች ትብብራቸውን የማጠናከር ጽኑ ፍላጎት አላቸው። የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከእርስ በእርስ ግንኙነት ባለፈ የአፍሪካ እና ህንድ እንዲሁም የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። ከ2000 ዓመት በፊት የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ጠንካራ እና ጽኑ ትብብር ተቀይሯል። በማይናወጥ መሰረት ላይም ቆሟል። የበለጠ ጥልቀቱ እየጨመረ የመጣው የሀገራቱ ግንኙነት በጋራ ብልጽግና፣ ስትራቴጂካዊ ትስስር፣ ዘላቂ ልማት እና የሀገራቱን ዜጎች ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ ቁርጠኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 975
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው። እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም። የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል። የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል። ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!