ENA - ኢዜአ አማርኛ
               አርእስተ ዜና
              
             
                       ኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ዓለም አቀፋዊ ህጎችን ተከትላ በሰላማዊ መንገድ ወደ ቀይ ባህር እንድትመለስ እንሰራለን - የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት
                      
 
                     
                      Oct 31, 2025 100
                     
 
                      
                       አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ዓለም አቀፋዊ ህጎችን ተከትላ በሰላማዊ መንገድ ዳግም ወደ ቀይ ባህር እንድትመለስ አበክረን እንሰራለን ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ በዓለም ላይ ከባህር በር በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆና ወደብ የሌላት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ መሆኗን በመግለጽ፤ ምክር ቤቱ ታሪካዊና ህጋዊ ጥያቄዋ ምላሽ እንዲያገኝ ሚናውን እንደሚወጣ ነው የገለፁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ እንደገለጹት፤ የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና የአካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ፤ ቀይ ባህር ኢትዮጵያ ፍትሕ ያጣችበት አጋጣሚ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ የባህር በር የኢትዮጵያ ህዝብ የተቀማ ሀብቱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሳትፈለግ ያጣችውን የባህር በር በድርድርና በሰላማዊ መንገድ እንዲመለስላት ፍትሐዊ ጥያቄ አቅርባለች ቀና ምላሽ ይገባታል ብለዋል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ኮሚቴ አባል አብርሃም በርታ (ዶ/ር) በዓለም ላይ ከባህር በር በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆና ወደብ የሌላት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ መሆኗን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ዓለም አቀፋዊ ህጎችን ተከትላ በሰላማዊ መንገድ ዳግም ወደ ቀይ ባህር መመለስ ይገባታል ብለዋል፡፡ በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ መነሻ በማድረግ የውጭ ግንኙነቶችን እንደሚወስን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ህጋዊና ታሪካዊ ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ እንዲያገኙ አስፈላጊ አዋጆችን በማጽደቅ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ድምጽ በማሰማትና የጋራ ውሳኔ በማስተላለፈ ለተፈጻሚነቱ አበክሮ ይሰራል ብለዋል፡፡
                      
 
                    
                       ኢትዮጵያ የምታዘጋጀው የሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ
                      
 
                     
                      Oct 31, 2025 64
                     
 
                      
                       አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የምታዘጋጀው የሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል ዛሬ ይፋ ሆኗል። 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ በ2026 በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይከናወናል። በውድድሩ ላይ የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበራት ምክር ቤት(ሴካፋ) ዞንን ወክለው የሚሳተፉ ሁለት ሀገራት የሚለዩበት የማጣሪያ ውድድር በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ከህዳር 6 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ሴካፋ የማጣሪያ ውድድሩ የምድብ ድልድል ዛሬ በዩጋንዳ ይፋ አደርጓል። በምድብ አንድ አዘጋጇ ኢትዮጵያ ከሶማሊያ፣ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሩዋንዳ ጋር መደልደሏን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ዩጋንዳ፣ ታንዛንያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን እና ብሩንዲ በምድብ ሁለት የተደለደሉ ሀገራት ናቸው። ውድድሩ በአበበ ቢቂላ እና ድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየሞች ይካሄዳል። በማጣሪያው ለፍጻሜ የሚያልፉት ሁለት ሀገራት የሴካፋ ዞንን ወክለው ለአፍሪካ ዋንጫ ያልፋሉ። እ.አ.አ በ2026 በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇ ሞሮኮን ጨምሮ 16 ሀገራት ይሳተፋሉ።
                      
 
                    
                        የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ቃል ኪዳን እና የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጉዞ 
                      
 
                     
                      Oct 31, 2025 64
                     
 
                      
                       ብዝኃ ህይወት ሁሉንም ሥነ-ሕይወታዊ ኃብቶች፣ እፅዋት፣ እንስሳትና ደቂቅ አካላት እንዲሁም በውስጣቸው የያዟቸው ዘረ-መሎችና እነዚህ የሚፈጥሯቸውን ውህዶች የሚያካትት ነው። የሁሉም ስርዓተ ምህዳር እና የሰው ልጆች የመኖር መሰረት ነው ብዝሃ ህይወት። እንደ አንዳንድ ጥናቶች ከሆነ በዓለማችን ካሉ ህይወት ካላቸው 8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዝርያዎች መካከል 80 በመቶዎቹ ገና ያልተገኙ ናቸው። የዓለም ብዝሃ ህይወት ቁልፍ ጠቀሜታዎች አሉት። የምግብ ምርታማነት፣ ንጹህ ውሃ እና አየር፣ ለርክበብናኝ (ፖሊኔሽን) እና አየር ንብረትን መቆጣጠርን ጨምሮ በርካታ ጠቃሜታዎች እንዳሉት የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ብዝሃ ህይወት ከ44 ትሪዮን ዶላር በላይ ወይም የዓለምን ዓመታዊ 50 በመቶ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) ይሸፍናል። የዓለም የብዝሃ ህይወት እና የስነ ምህዳር አገልግሎቶች የበይነ መንግስታት የሳይንስ ፖሊሲ መድረክ ((IPBES) በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ በሰው የተለያዩ ተግባራት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የመሬት አጠቃቀም ምክንያት አንድ ሚሊዮን ገደማ ህይወት ያላቸው ዝርያዎች ሊጠፉ እንደሚችሉ ስጋቱን አስቀምጧል። በዚህ የዓለም ቀውስ ውስጥ አፍሪካ የብዝሃ ህይወት እምቅ ሀብቶች ያላት አህጉር ሆና ተገኝታለች። የብዝሃ ህይወቱ በርካታ እና ጫና መቋቋም የሚችሉ የአይበገሬነት አቅም ያላቸው ናቸው። የዓለም አንድ አምስተኛ እጽዋት፣ አጥቢ እንስሳት እና አዕዋፋት የሚገኙት በአፍሪካ ነው። ከ50 ሺህ በላይ የእጽዋት ዝርያዎች፣ 1 ሺህ 100 አጥቢ እንስሳት፣ 2 ሺህ 500 የአዕዋፋት እና ከ3000 በላይ የአሳ ዝርያዎች ይገኛሉ። የዓለማችን ሁለተኛው ጥብቅ ደን የኮንጎ ጥቅጥቅ ደን፣ የቦትስዋና ኦካንጋቮ ዴልታ፣ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ስፍራዎች እና የማዳጋስካር ልዩ ስነ ምህዳሮችና ዝርያዎች ከአፍሪካ ዋነኛ ብዝሃ ህይወቶች መካከል ይጠቀሳሉ። የአፍሪካ ብዝሃ የኔዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ ከማሻሻል ባለፈ የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት በዘላቂነት ማስቀጠል የሚችል አቅም ያለው ነው። ይሁንና የአፍሪካ ብዝሃ ህይወቶች ለተለያዩ ፈተናዎች የተጋለጡ ናቸው። አህጉሪቷ በየዓመቱ 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር ገደማ ደን እንደምታጣ መረጃዎች ያሳያሉ። እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ህዝብ ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቀው የአፍሪካ ህዝብ፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ህገ ወጥ አደን ፣ ዘላቂነት የጎደለው የመሬት አጠቃቀም እና ብክለት የአህጉሪቷን ብዝሃ ህይወት ስርዓት እየጎዱ ይገኛሉ። የአፍሪካ ጥብቅ ስፍራዎች ለማስተዳደር በዓመት ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያስፈልግ ቢሆንም አንዳንድ ሀገራት በቂ ኢንቨስመንት እየመደቡ አይገኝም። አፍሪካ የሶስትዮሽ ተፈጥሯዊ ቀውሶችን እያስተናጋደች ትገኛለች ማለት ይችላል። የብዝሃ ህይወት መመናመን፣ ብክለት እና የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ተግዳሮቶች ናቸው። የአስተዳደር ስርዓት አለመጠናከር፣ የተገደበ የፋይናንስ አቅርቦት እና የአካባቢ ማህበረሰብ መሪዎች በውሳኔ መስጠት ውስጥ አለመሳተፋቸው በዋናነት የሚጠቀሱ ፈተናዎች እንደሆኑም ይነገራል። የአፍሪካ ሀገራት የብዝሃ ህይወት ችግሮችን ለመፍታት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛል። ከነዚህም አንዷ ኢትዮጵያ ናት። ኢትዮጵያም ከፍተኛ የብዝኃ ሕይወት ኃብት ካላቸው አገራት መካከል አንዷ ናት። አሁን ላይ አገሪቱ ከ6 ሺህ በላይ የእፅዋት ኃብቶች ያላት ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ 600 ወይም 10 በመቶ የሚሆኑት በአገሪቱ ብቻ የሚገኙ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢንስቲትዩት መረጃ ያመለክታል።   ጎን ለጎንም የወፍ ዝርያዎችን ጨምሮ በየብስና በውኃ አካላት ውስጥ የሚኖሩ የተለያዩ ዓይነት ዝርያ ያላቸው በርካታ እንስሳት በኢትዮጵያ ይገኛሉ። ይሁንና የየብስና የውኃማ አካላት አካባቢ መለወጥ ለእነዚህ ብዝኃ ሕይወት ኃብቶች ሥጋት እየሆነ መምጣቱን ነው ኢንስቲትዩቱ የገለጸው። በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለትና ዘለቄታዊ ያልሆነ የተፈጥሮ ኃብት አጠቃቀም ለብዝኃ ሕይወት ኃብቶች መመናመን ምክንያቶች ናቸው። የሕዝብ ቁጥር መጨመርን ተከትሎ ደን ወደ እርሻ መሬትነት መቀየር እንዲሁም መጤ ወራሪ አረሞች ነባር አገር በቀል ዝርያዎች የሚበቅሉበትን ሥፍራ መያዝም ሌላኛው ምክንያት ነው። ይህንንም ተከትሎ ወይራ፣ ዝግባ፣ ቀረሮ፣ ዋንዛ፣ ጥቁር እንጨትና ኮሶ እየተመናመኑ ካሉ የእፅዋት ብዝኃ ሕይወት ዝርያዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ዝርያዎቹ አንዴ ከጠፉ መልሰው የማይገኙ በመሆናቸው ኢንስቲትዩቱ ዝርያዎቹን የማራባትና የማብዛት ሥራ በልዩ ትኩረት እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። ከእነዚህም በተጨማሪ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውና በኢትዮጵያ ብቻ ያሉ የእፅዋትና እንስሳት ብዝኃ ሕይወት ዝርያዎችን የመጠበቅ ሥራ እየተከናወነ ነው። በዚህም የቀረሮ የእጽዋት ዝርያ የማብዛት ሥራ እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች የተመናመኑ የዳልጋ ከብቶች ወደ ነበሩበት የመመለስ ሥራም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። በተመሳሳይ "የሸኮ ዳልጋ ከብት" እየተባለ የሚጠራውን ዝርያ የማብዛት እንዲሁም በጣና ኃይቅ የዓሳ ዝርያዎች ላይ ያለውን መመናመን ለመቀልበስም የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ነው ኢኒስቲትዩቱ ያስታወቀው። ጥብቅ አካባቢዎችን የማስፋት፣ የእፅዋት አፀድ ጥበቃ፣ የዘረመልና የማኅበረሰብ የዘር ባንኮችን በየአካባቢው የማስፋት ተግባርም እየተሰራ መሆኑን አመልክቷል። የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብርም የብዝኃ ሕይወትን ከመጠበቅና ከማስቀጠል አኳያ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ያሏትን የብዝኃ ሕይወት ሃብቶች የመጠበቅ ተልዕኮ የተሰጠው የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩትም ኃብቶቹን የማንበር (የመጠበቅ)፣ ዘለቄታዊ አጠቃቀምና ፍትሃዊ የጥቅም ተጋሪነት ላይ እየሰራ ይገኛል። በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎች እና ቀጣይ እርምጃዎች የሚመክር ጉባኤ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ከጥቅምት 23 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ቃል ነው። ጉባኤው ለአፍሪካ ብዝሃ ህይወት መመናመን፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ብክለት የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ መስጠት የሚያስችል መድረክ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። የአፍሪካ ቀዳሚ የብዝሃ ህይወት አጀንዳዎች ምክክር ይደረግባቸዋል። አህጉር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ትስስርን ማጠናከር እና ለብዝሃ ህይወት ክብካቤ የፋይናንስ ሀብትን በተቀናጀ ሁኔታ ማሰባሰብ ሌሎች የጉባኤው አጀንዳዎች ናቸው። ኢትዮጵያ እና የጉባኤው አዘጋጅ ቦትስዋን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት በብዝሃ ህይወት ጥበቃ እያከናወኗቸው ያሉ ስራዎችን አስመልክቶ ልምዳቸውን ያጋራሉ። እ.አ.አ በ2026 በአርሜኒያ በሚካሄደው 17ኛው የዓለም የብዝሃ ህይወት ጉባኤ (ኮፕ 17) ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች የአፍሪካን ድምጽ በጋራ ማሰማት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ይደረጋል። ጉባኤው አንድ ብዝሃ ህይወት የልማት አቅም ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ብልጽግና አረጋጋጭ ሞተር መሆኑ ግልጽ መልዕክት የሚተላለፍበት መድረክ ነው። ፍላጎቶች ተጨባጭ እና መሬት ወደወረዱ መፍትሄዎች ማውረጃ አማራጭ ሆኖም ያገለግላል። በአርሜኒያ ለሚገሄደው ዓለም አቀፍ ጉባኤ አፍሪካ ፍትሃዊ የፋይናንስ አቅርቦት እንድታገኝ፣ ሁሉን አቀፍ የብዝሃ ህይወት አስተዳደር እንዲረጋገጥ እና ለፍትሃዊ የጥቅም ተጋሪነት ድምጿን ለማሰማት ስንቅ ለሚሆን የሚያስችል አህጉራዊ መድረክ ጭምር ነው ማለት ይቻላል። በአፍሪካ ያለውን የብዝሃ ህይወት አቅም በውጤታማ የአስተዳደር ስርዓት፣ አካታች የማህበረሰብ ተሳትፎ እና ዓለም አቀፍ ትብብር አማካኝነት ወደ ዘላቂ እድገት ምንጭነት ማሸጋገር እንደሚቻል ጥርጥር የለውም። የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ስራ ለዓለም የብዝሃ ህይወት ግቦች መሳካት ትልቅ አበርክቶ ይኖረዋል። በብዝሃ ህይወት ላይ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ለአፍሪካ መጻኢ ጊዜ መሰረት እንደመጣል ይቆጠራል።
                      
 
                    
                       የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች ለወጣቶች ሰፊ የስራ ዕድልን በመፍጠር ተጠቃሚነታችንን የሚያሳድጉ ናቸው- ወጣቶች
                      
 
                     
                      Oct 31, 2025 61
                     
 
                      
                       ጎንደር/ ገንዳ ውሃ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የወጠነቻቸው የልማት ፕሮጀክቶች ለወጣቶች ሰፊ የስራ ዕድልን በመፍጠር ተጠቃሚነታችንን የሚያሳድጉ ናቸው ሲሉ የጎንደርና ገንዳ ውሃ ከተሞች ወጣቶች ገለጹ። የጎንደርና የገንዳ ውሃ ከተሞች ወጣቶች በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄደዋል፡፡ በጎንደር ከተማ በተካሄደው መድረክ የተሳተፈው ወጣት ደሴ ማለደ እንደገለጸው በአገራችን ሊካሄዱ የታቀዱ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ወጣቶች በሀገራቸው ሰርተው እንዲለወጡ የሚጨበጥ ተስፋን የሚሰጡ ናቸው።፡ በቅርቡ ይፋ የተደረጉት የጋዝ ማምረቻና የነዳጅ ማጣሪያ፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የአውሮፕላን ማረፊያና ሌሎች ፕሮጀክቶች ለወጣቱ ሰፊ የስራ ዕድልን በማመቻቸት ለፕሮጀክቶቹ ስኬት የተለየ አበርክቶ እንዲኖረው ያደርጋሉ ብሏል።   የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪው ወጣት ጀማል መሃመድ በበኩሉ በሀገራችን የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች እንዲሳኩ እኛ ወጣቶች ሰላማችንን በመጠበቅና አንድነታችንን በማጠናከር በህብረት እንሰራለን ሲል ተናግሯል። መንግስት ለግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የሰጠው ትኩረት ወጣቱ ሰፊ የስራ እድል አንዲያገኝ ምቹ መደላድልን የሚፈጥር በመሆኑ የአካባቢያችንን ሰላም በማዝለቅ ፕሮጀክቶቹ እውን እንዲሆኑ እንሰራለን ብሏል። የሰላምና ልማት መረጋገጥ በቀጥታ የወጣቱን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው ያለው ደግሞ ሌላው የከተማው ወጣት አስማረ ማለደ ነው። በዚህም መንግስት ሰላምና ልማትን በማረጋገጥ የአገራችን እድገት ለማፋጠን በሚያደርገው ጥረት በንቃት በመሳተፍ የራሱንና የሌሎች ወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማስፋት እንደሚሰራም ተናግሯል። ወጣት ኤርሚያስ አቡሃይ በበኩሉ "እኛ ወጣቶች የሀገራችንን እድገትና ብልፅግና በማረጋገጥ ያለንን ህልምና ተስፋ ለማሳካት መስራት ይጠበቅብናል ብሏል፡፡ ሌላኛዋ የመድረኩ ተሳታፊ ወጣት ሙሉ ተገኘ በበኩሏ ፅንፈኝነትን በማውገዝና በመታገል በአካባቢው የተጀመሩ የልማትና የህግ ማስከበር ተግባራት እንዲሳኩ ኃላፊነቷን እንደምትወጣም ገልፃለች።   የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተወካይ አቶ ነጻነት መንግስቴ እንደገለጹት የኢትዮጵያን ማደግና መለወጥ የማይሹ የውስጥና የውጪ ሃይሎች የሚፈጥሩትን ሴራ በማክሸፍ ወጣቱ ታሪካዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡ የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለወጣቱ ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ጠቁመው ለስኬታቸው የጋራ ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል። የገንዳውሃ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች፣ ባህልና ስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኪሩቤል መንግስቴ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለውን አንፀባራቂ የልማት ድሎችን ለማስቀጠል የወጣቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነው። ሀገራችንን ቀዳሚ እንድትሆን ለሚያደርጉ ሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ወጣቱ ትውልድ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣም አሳስበዋል። በተካሄዱት የውይይት መድረኮች ላይም የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ወጣቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።  
                      
 
                    
                       በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ አበረታች የልማት ተግባራት እንዲጠናከሩ የድርሻችንን እንወጣለን -የተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎች
                      
 
                     
                      Oct 31, 2025 66
                     
 
                      
                       ወላይታ ሶዶ/ሀዋሳ/ጂንካ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):- በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ አበረታች የልማትና የሰላም ማስከበር ተግባራት እንዲጠናከሩ የድርሻቸውን እንደሚወጡ በወላይታ ሶዶ፣ ሀዋሳና ጂንካ ከተሞች ነዋሪዎች ተናገሩ። በሀገሪቱ ወቅታዊ የልማትና ሰላም ግንባታ ዙሪያ ኢዜአ በየከተሞቹ ነዋሪዎችን አነጋግራል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ አቶ ነጋ አንጎሬ፤ እንደ ሀገር እየተካሄዱ ያሉ የልማትና የሰላም ግንባታ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም ተጀምረው የማይጠናቀቁ የልማት ስራዎች የመልካም አስተዳደር ችግር ሆነው የቆዩትን ከለውጡ ወዲህ በመሻሻል መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት መቻሉን አንሰተዋል። ይህም ነባር ፕሮጀክቶችን ከማጠናቀቅ ጎን ለጎን በአዲስ አስተሳሰብ የሚጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት እየተጠናቀቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። እንደ ሀገር አሁን ላይ በሰላም ግንባታና በልማት መስክ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ለትውልድ የሚተላለፉ በመሆናቸው ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚውጡ ተናግረዋል። በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞችም ሆነ ገጠር አካባቢዎች እየታየ ያለው የልማት እንቅስቃሴ የተሻለች ኢትዮጵያን እንድናይ መሰረት እየጣለ ነው ያሉት ደግሞ ሌላው የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ አቶ ከበደ ኤሌ ናቸው። ለዚህም የኮርደር ልማት፣ የወንዝ ዳር ልማትና አረንጓዴ አሻራን ለአብነት ጠቅሰዋል። ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት ነው ያሉት አቶ ከበደ፤ መንግስት በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም ሰፍኖ ልማት እንዲፋጠን እያከናወናቸው ያሉት ውጤታማ ተግባራት የሚያኮሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ተካልኝ አባ እንዳሉት፤ መንግስት ለሰላም ግንባታና ለልማት በሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ ነው። በከተሞች እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ብቻ ሳይሆን የሀገር ገጽታን የቀየረና የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያሳለጠ መሆኑን ጠቅሰዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ፣ እንደሀገር ግንባታቸው የተጀመሩ የማዳበሪያ ፋብሪካ ጨምሮ ግዙፍ ፕሮጀክቶች በሀገር ኢኮኖሚ እድገት ላይ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አመልክተዋል ። እንደሀገር የተጀመሩ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ የሚያሳዩ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ ሌላዋ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሙዳይ ደመቀ ናቸው። ሀገራዊ የልማት ስራዎች የዜጎችን በሀገር ሰርቶ የመለወጥ እድል ያሰፉና ትውልድን የሚየሻገሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የጂንካ ከተማ ነዋሪ አቶ ዳኜ ዮሴፍም፤ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። የባሕር በርን ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝና ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች እንዲሳኩ ከመንግስት ጎን በመሆን የድርሻዬን እወጣለሁ ያሉት ደግሞ የከተማው ነዋሪ አቶ ጋሻው ገላው ናቸው።
                      
 
                    
                  ፖለቲካ
                 
                
                          እየተከናወነ ባለው የሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፏችንን ይበልጥ እናጠናክራለን - የባሕርዳር ወጣቶችና ሴቶች
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 72
                        
 
                         
                          ባሕር ዳር፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፡- በከተማው እየተከናወነ በሚገኘው የሰላም ግንባታና የልማት ተግባራት ላይ ተሳትፏቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የባሕርዳር ከተማ ወጣቶችና ሴቶች ተናገሩ። የከተማው ወጣቶችና ሴቶች በሰላም ማፅናት ዙሪያ ዛሬ በባሕርዳር ከተማ ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊ ትዕግስት አባቡ በሰጠችው አስተያየት፤ መንግስት ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት በማብቃት የሚደነቅ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብላለች። የልማት ስራዎቹ የወጣቶችንና ሴቶችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ጠቅሳ፤ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አንስታለች። ለልማት ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላም ግንባታ ተሳትፎዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል ተናግራለች። ሌላው ተሳታፊ አዲሱ ዳኘው በበኩሉ፤ ከለውጡ ወዲህ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የወጣቶችና ሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ምቹ መደላደል የፈጠሩ ናቸው ብሏል። እየተከናወኑ የሚገኙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሃገሪቱን ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ደረጃ የሚያሸጋገሩ እንደሆኑም ተናግሯል። የልማት ስራዎቹ የተከናወኑት ከሰላም ግንባታ ጎን ለጎን መሆኑን ጠቅሶ፤ የልማት ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲቻል ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጿል።   የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ሃላፊ ቶማስ ታምሩ፤ ከለውጡ ወዲሕ በከተማው የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተለይም ከተማዋን ለቱሪስቶችና ነዋሪዎች ምቹ በማድረግ በኩል የኮሪደር ልማት ስራው ለአብነት የሚጠቀስ ዋና ተግባር ነው ብለዋል። ሌሎች የሕዝብ ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ለዚህም የከተማው ወጣቶችና ሴቶች ድጋፍና ትብብር የጎላ መሆኑን አንስተዋል። የተጀመሩ የልማት ስራዎች የወጣቶችንና የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ተጠቃሚነት የበለጠ እንዲያሳድጉ የሰላም መፅናት ወሳኝ በመሆኑ ሴቶችና ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው አፅንኦት ሰጥተዋል።   በከተማ አስተዳደሩ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር ዓይን ገላጭ የሆኑ አበረታች የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች፣ ሕፃናትና ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ ሰብለ ዘውዱ ናቸው። ከተማዋ በተፈጥሮ ያላትን ፀጋ በኮሪደር ልማት በማጉላት ከጣና ሃይቅ ጋር ያላት ትስስር ላቅ ወዳለ ደረጃ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
                         
 
                       
                          የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ የልማት ተግባራት እንዲሳኩ የበኩላችንን እንወጣለን -ወጣቶች
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 72
                        
 
                         
                          ደሴ/ወልድያ/ ሰቆጣ፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፡- የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ የልማት ተግባራት ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚወጡ በአማራ ክልል ወጣቶች ገለጹ። "ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ወጣቶች የተሳተፉባቸው የውይይት መድረኮች በደሴ፣ ወልዲያና ሰቆጣ ከተሞች ዛሬ ተካሂደዋል። ከደሴው መድረክ ተሳታፊዎች ውስጥ ወጣት ከድር የሱፍ በሰጠው አስተያየት፤ መንግስት ሰላምን ከማፅናት ጎን ለጎን የሚያካሂዳቸው ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለወጣቶችና ለቀጣዩ ትውልድም ተስፋ የሰጡ ናቸው ብሏል። ፕሮጀክቶቹ የሀገሪቱን እድገት በማፋጠን መሰረታዊ ለወጥ የሚያመጡ መሆናቸውን ጠቅሶ፤ ከሌሎች ወጣቶች ጋር በመተባበር ሰላም በማስጠበቅ ለአካባቢው ልማት ብሎም ለሀገራዊ ፕሮጀክቶች ስኬታማነት የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ሌላዋ የመድረኩ ተሳታፊ ወጣት ቤተልሔም ፈንታው በበኩሏ፣ የማዳበሪያ፣ የጋዝ፣ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያና ሌሎች ፕሮጀክቶች መገንባት ለመጪው ትውልድ ትልቅ ተስፋ የሰነቁ ናቸው ብላለች። በዚህ ሂደት ፕሮጀክቶቹ ተሳክተው የሀገራችንን ብልጽግና ለማረጋገጥ የድርሻችንን ለመወጣት ቁርጠኛ ነን፤ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጅት ሰላማችንን ለማጽናት የጀመርነውን ስራ እናስቀጥላለን ብላለች።   የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተወካይና የሕዝብ ግንኙነት ምክትል አማካሪ አቶ አወል አህመድ በበኩላቸው፤ የከተማውን ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ ከወጣቱ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የወል ትርክትን በማስፈን ሕብረብሔራዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ወጣቶች የጀመሩትን የነቃ ተሳትፎ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።   በተመሳሳይ በወልዲያው መድረክ ከተሳተፉት መካከል ወጣት አቤል አያሌው፤ የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ ልማት ይበልጥ እንዲጠናከር የድርሻችንን ለመወጣት መንቀሳቀስ አለብን ብሏል። ሰላምን በማፅናት የአካባቢውና ሀገራዊ ተስፋ ሰጪ የልማት ተግባራት ከፍጻሜ እንዲደርሱ በጋራ መነሳት አለብን ያለው ደግሞ ወጣት ኃይለማሪያም ስዩም ነው። የወልድያ ከተማ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሀላፊ አቶ መላኩ ዓለሙ፤ ጽንፈኛ ቡድኑ የባዕዳን ተላላኪ በመሆን ታሪክ የማይረሳው አፍራሽ ድርጊት ለመፈፀም ቢሞክርም በፀጥታ ሀይሉ እየመከነበት በመበታተን ላይ መሆኑን አብራርተዋል። ሰላምን በዘላቂት አፅንቶ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት ወጣቶች ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።   በሌላ በኩል በሰቆጣው ውይይት የተሳተፈው ወጣት ጥላሁን አበበ፤ መንግስት ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ እያደረገ ያለው ጥረት እንደግፋለን ብሏል። ሌላው ተሳታፊ ወጣት አስፋው ገብረ መድህን በበኩሉ፤ ለሰላም መስፈን እኛም ከመንግስት ጎን ተሰልፈን የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉ ገልጿል። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ በበኩላቸው፤ በአካባቢ የሰፈነውን ሰላም አስጠብቆ በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ብሎም የፀጥታ አካላት እያደረጉት ያለው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገራችን ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች ላይ አተኩራለች ያሉት አቶ ጌትነት፤ በቀጣናው ያላትን ተሰሚነት ለማጠናከር ወጣቶች ሚናቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል። በከተሞቹ በተካሄደው የውይይት መድረኮች የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ ወጣቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
                         
 
                       
                          የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች ላይ በማተኮር ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል 
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 157
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች ላይ በማተኮር ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። መገናኛ ብዙኃን የሚያመነጯቸው መረጃዎች ግንዛቤን በመፍጠር፣ የሀገር ገጽታ በመገንባት፣ የዕቅድና ፖሊሲዎችን በማስተዋወቅ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ቁልፍ ሚና አላቸው። በዜጎች መካከል የሚንጸባረቁ በብዝኅነት ላይ የተመሰረቱ እሳቤዎች የሚስተናገዱበትን አጀንዳ በመቅረጽም አሰባሳቢ ትርክት ግንባታን በማስተጋባት ብሔራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ ወሳኝ መሳሪያዎች ናቸው። የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ሀገራዊ መግባባትን ለማጠናከር የመገናኛ ብዙኅን ሙያዊ ሥነ-ምግባርና ኃላፊነት ለዘላቂ ዕድገትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የዘርፉ ምሁራንም መገናኛ ብዙኅን በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስጠበቅ ሙያዊ ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት መምህር ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር)፤ የየትኛውም ዓለም የመገናኛ ብዙኅን የሚሰራው ለተመሰረተበት ሀገር ብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ነው ብለዋል።   በኢትዮጵያ ጉዳይ መረጃዎችን የሚያመነጩ መገናኛ ብዙኅንም ዜጎችን የሚያቀራርቡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለሀገር ዕድገት መፋጠን አቅም የሚሆኑ ዘርፎች ላይ መስራት እንደሚኖርባቸው መክረዋል። በዚህም መገናኛ ብዙኅን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስከብሩ አጀንዳዎችን በመቅረጽ ለዜጎች ሁለንተናዊ ትሥሥር በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ህዝብና መንግስትን በማቀራረብ የሀገርን የዕድገት ፖሊሲ በማስተዋወቅ የትግበራ ሂደታቸው ለዜጎች ህይወት ሁለንተናዊ ለውጥ መዋሉን ተከታትሎ የማረጋገጥ ስራ ማከናወን እንደሚጠበቅም አንስተዋል። በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር መንግስት ለብሔራዊ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት ድህነትን ለመቀነስ የሚኖራቸውን ጉልህ ፋይዳ ማሳየት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል። በተለይም የኢትዮጵያን ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ የቀይ ባሕር ባለቤትነት ብሔራዊ ጥቅም ላይ ምክንያታዊ ዘገባዎችን ማስተጋባት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። በሠመራ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ አስፈፃሚና የጋዜጠኝነት ትምህርት ክፍል መምህር መሐመድ አህመድ፤ ኢትዮጵያዊያን በብሔራዊ ጥቅምና ሀገራዊ ፍላጎቶች ላይ ልዩነት ሊኖረን አይገባም ብለዋል።   የኢትዮጵያዊያን የአንድነት አሻራ ያረፈበት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ስኬትም ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር አሰባሳቢ ትርክት መገንቢያ ግዙፍ ብሔራዊና አህጉራዊ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የብሔራዊ ጥቅም መሠረት የሆነው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም የዜጎች የጋራ ብሔራዊ አጀንዳ መሆኑን አስገንዝበዋል። በሁሉም የመገናኛ ብዙኅን አማራጮች መረጃን የሚያመነጩና የሚያሰራጩ ዜጎችም ሀገራዊ መግባባትና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ የልማት አጀንዳዎች ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ መክረዋል።
                         
 
                       
                          የባህር በር ጥያቄ የሀገር ህልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ እንሰራለን- የጋራ ምክር ቤቱ
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 104
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-የባህር በር ጥያቄን የሀገር ህልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ አድርጎ ለተግባራዊነቱ እንደሚሰራ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን ማለታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም፤ ለጎረቤቶቻችን መናገር የምንፈልገው ኢትዮጵያ ስታደግ ለቀጣናው ልማት ምንጭ ትሆናለች፤ የምንፈልገው በትብብር ማደግ ነው፤ በመሆኑም የባህር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው በማለት አጽንኖት ሰጥተው ተናግረዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራሮች የባህር በር ጥያቄ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊ እውነታዎችን መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት የባህር በር የነበራት፣ በቀጣናው ጂኦፖለቲካዊ እንቅስቃሴም ጉልህ ተሳትፎ የነበራት ሀገር መሆኗን አስታውሰው ባለፉት 30 ዓመታት ያለባህር በር የቆየችበት ጊዜ የሚያስቆጭ መሆኑን አንስተዋል።   ባህር በር ኢትዮጵያ ከድህነት የምትወጣበት፣ በቀጣናው የዲፕሎማሲ ከፍታዋን የምታረጋግጥበት፣ ንግዷን የምታሳልጥበት ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ በምክር ቤቱ ይደግፋል ያሉት የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ ናቸው። ጉዳይ የአገር አጀንዳ እንዲሆን ላደረጉት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምስጋና እንደሚገባቸው አንስተው ጥያቄው የኢትዮጵያን ህልውና ማረጋገጫ ዋና መሳሪያ ነው ብለዋል። ሁሉም የፖለቲካ ተዋናዮችና መላው ህዝብ የባህር በር ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ በጋራ በመቆም ታሪካዊ ስራ መስራት አለበት ነው ያሉት። የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ጸሃፊ አቶ ታሪኩ ድምበሩ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ አጀንዳ ሆኖ መምጣቱ ወሳኝና መሰረታዊ ጉዳይ በመሆኑ መንግስት ሊመሰገን ይገባል ብለዋል።   የባህር በር ጥያቄው የቅንጦት ሳይሆን የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑን በማመን የምክር ቤቱ ጠቅላላ ጉባኤ የጉዳዩ አስፈላጊነትና ወቅታዊነት ላይ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ ለተግባራዊነቱ የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የባህር በር የሀገር ህልውና እና የትውልድ ጥያቄ በመሆኑ የትኛውም የፖለቲካ ተዋናይ ይህንን እውነታ እና የሀገር ብሄራዊ ጥቅም የሚዘነጋው አይሆንም ያሉት የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ጸሃፊ ለምላሹ የጋራ ጥረታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ 22 የፖለቲካ ፓርቲዎች አባል የሆኑበት የጋራ ምክር ቤቱ የባህር በር ጥያቄን የሀገር ህልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ አድርጎ የሚወስደው እና ለምላሹም የሚሰራ መሆኑን አረጋግጧል።
                         
 
                       
                          ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) ለምክር ቤት አባላት የሰጡት ማብራሪያ የትግራይ ክልል ህዝብን የሰላምና የልማት ፍላጎት በትክክል ያመላከተ ነው- የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 140
                        
 
                         
                          መቀሌ ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለምክር ቤት አባላት የሰጡት ማብራሪያ የትግራይ ክልል ህዝብን የሰላምና የልማት ፍላጎት በትክክል ያመላከተ መሆኑን የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወቃል። በተለይም በሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ላይ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እና መንግስት ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በተመለከተ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው የትግራይ ክልል ህዝብ ፍላጎት ዘላቂ ሰላም እና የልማት ተጠቃሚነት መሆኑን ገልጸው የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ በዚህ የፌዴራል መንግስት ብዙ መስራቱን አንስተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምክር ቤት አባላት የሰጡት ማብራሪያ የትግራይ ክልል ህዝብን የሰላምና የልማት ፍላጎት በትክክል ያመላከተ መሆኑን ገልጸዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል ወጣት ይልማ ሃብቴ፣ አቶ አፅበሃ አብርሃ እና መምህር ሃይለ ከለለው፤ የትግራይ ክልል ህዝብ ለግጭትና ለጦርነት የሚሰሩ አካላትን በፍጹም አይቀበልም ብለዋል።   የህዝቡ ፍላጎት ከምንም በላይ ሰላም እና ልማት መሆኑን ተናግረው ይህንን ፍላጎቱን በአግባቡ ተገንዝቦ የሚሰራለት አስተዳደር የሚሻ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የወጣቱ ፍላጎት ሰርቶ መለወጥና ህይወቱን በአግባቡ መምራት መሆኑን የተናገረው ወጣት ይልማ፤ በክልሉ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቋል። የትግራይ ክልል ህዝብ ፍላጎት ሰላሙን በመጠበቅ ለሀገር ልማት በጋራ መስራትና መጠቀም በመሆኑ ለተግባራዊነቱ የድርሻችንን ለመወጣት እንሰራለን ብሏል። በመቀለ የዓዲሐ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር ሃይለ ከለለው በበኩላቸው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለልማት ስኬት እና ለሰላም ግንባታ እያደረጉት ያለው ቀናኢነት የሚደነቅ ነው ብለዋል።   የትግራይ ክልል ህዝብም የሚሻው ይህንኑ መሆኑን ያነሱት መምህሩ የህዝቡን ፍላጎት በተረዳ መልኩ ለምክር ቤቱ የሰጡት ማብራሪያ ተገቢና ትክክለኛ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ አፅበሃ አብርሃ፤ በሁሉም መልኩ የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግ መንግስት እያከናወናቸው ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ትልቅ ተስፋ የተሰነቀባቸው መሆኑን ተናግረዋል።   በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች ሰላምን በማጽናት ልማትን በማስቀጠል የጋራ ልማትና ተጠቃሚነታችንን እውን ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል። ከትግራይ ክልል ጋር በተገናኘ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡት ማብራሪያም የክልሉን ህዝብ የሰላምና የልማት ፍላጎት መሰረት ያደረገ እና ትክክለኛ ምልከታ መሆኑን ተናግረዋል።
                         
 
                       
                           የባሕር በር ጉዳይ ምላሽ ማግኘት ያለበት የጋራ ጥያቄያችን ነው- የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 116
                        
 
                         
                          ባሕር ዳር፤ ጥቅምት 21 /2018(ኢዜአ)፡ - የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ህልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ ማግኘት ያለበት የጋራ ጥያቄያችን ነው ሲል የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሀይል ንቅናቄ (አዴሀን) ሊቀመንበር ተስፋሁን አለምነህ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ህልውና እና የብሄራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ ማግኘት ያለበት የጋራ ጥያቄያችን ነው ብለዋል። የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርም በሀገር ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ የተለየ አቋም የሌላቸው መሆኑን አንስተው በዚህ ረገድ መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴና የያዘውን አቋም እናደንቃለን እንደግፋለንም ሲሉ አረጋግጠዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ ምክር ቤቱ በቅርበት እንደሚሰራ እና ህብረ ብሄራዊ አንድነቷና ብሔራዊ ጥቅሟ የተከበረች ሀገር ለልጆቻችን ለማስረከብ እንሰራለን ብለዋል። እንደፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለሰላም መስፈን፣ ለሕግ መከበርና ሌሎች የውስጥ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንደምንሰራ ሁሉ በብሔራዊ ጥቅሞችና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በጋራ መስራት ግዴታቸን ነው ብለዋል። መንግስት የባሕር በር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ ሲሰለፍ በተቃርኖ መቆም በታሪክ ተወቃሽ የሚያደርግና ለሕሊናም ሰላምን የሚነሳ መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከቀናት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ፤ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ የማይቀር ስለመሆኑ አስረግጠው መናገራቸው ይታወሳል።
                         
 
                       
                          ሰላምን በማጽናት ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እየተወጣን ነው
                         
 
                        
                         Oct 30, 2025 175
                        
 
                         
                          ደሴ/ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡-ሰላምን በማጽናት ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን የደሴ እና የደብረ ብርሃን ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ገለጹ። የደሴ ከተማ አስተዳደር "ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ዛሬ የውይይት መድረክ አካሂዷል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ወይዘሮ ሄለን አሰፋ እንደገለጹት፣ የከተማዋን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ከመንግስት ጎን በመሰለፍ የድርሻቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በደሴ ከተማ ሰላም መስፈኑ የንግድ ሥራቸውን ያለምንም ችግር ለማከናወንና ቤተሰባቸውን ለመምራት እንዳስቻላቸውም ገልጸዋል። የከተማዋን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ሂደት በንቃት ከመሳተፈ ባለፈ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል የከተማዋ ልማት እንዲፋጠን የድርሻቸውን መወጣታቸውን አስረድተዋል።   ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ አህመድ ጀማል በበኩላቸው ለጤናማ የንግድ እንቅስቃሴ የሰላም ዋጋ የማይተካ ነው ብለዋል። አሁን ላይ በአካባቢው ሰላም በመስፈኑ ምርትና ሸቀጣሸቀጥ ከሌላ አካባቢ ወደ ከተማዋ በማምጣት ሥራቸውን በአግባቡ ለማከናወን መቻላቸውን ተናግረዋል። በአካባቢያቸው የሰፈነውን ሰላም በመጠበቅ የንግድ ሥራቸውንና ልማትን ለማፋጠን ቁርጠኛ መሆናቸውን የገለጹት አቶ አህመድ፣ የታጠቁ ኃይሎችም የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ህብረተሰቡን መካስ እንዳለባቸው ተናግረዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ ካሳው በበኩላቸው የንግዱ ማህበረሰብ የደሴ ከተማና አካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ከመንግስት ጋር በትብብር የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።   ወጣቶችን ስለ ሰላም ከማስተማር በተጨማሪ ገበያው እንዲረጋጋ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ ዜና በደብረ ብርሀን ከተማ የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት የከተማቸውን ሰላም በማጠናከር ልማት እንዲፋጠን ከመንግስት ጎን ሆነው የሚያደርጉትን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። የከተማዋ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት በዘላቂ ሰላምና በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ከከተማው መስተዳድር ኃላፊዎች ጋር ዛሬ መክረዋል።   ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ንጉሴ ማሞ ሰላም ለሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ለከተማቸው ሰላም መጠናከር የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። የንግድ ስራቸውን ለማከናወንም ሆነ ከልማት ሥራዎች ተጠቃሚ ለመሆን ሰላም ወሳኝ መሆኑን እና በከተማቸው የሰፈነውን ሰላም ለማስቀጠል የህዝብ ትብብር አስፈላጊ ነው ብለዋል። የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻልና የልማት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ሰላምን ማጽናት አይነተኛ ሚና እንዳለው የገለጹት ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ ደግሞ አቶ ሳሙኤል አውግቸው ናቸው። የሰላም እጦት ያለውን ተጽዕኖ እናውቀዋለን ያሉት ነዋሪው፣ ለሸቀጦች ዋጋ መናርና መጥፋት አንድ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል።   የንግድ ሥራቸውን በተረጋጋ ሁኔታ ለማከናወንና ሁለንተናዊ ልማት እንዲፋጠን በከተማቸው የሰፈነውን ሰላም ለማጽናት ተግተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ለእዚህም እንደ ንግዱ ማህበረሰብ አባል ከመንግስት ጎን በመቆም የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። በተለይ ስለሰላም አስፈላጊነትና ሰርቶ ለመለወጥ ሰላም ያለውን ፋይዳ ለህብረተሰቡ የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። መንግስት የጀመራቸው የልማት ስራዎች ዳር እንዲደርሱና በሰላም ወጥቶ ለመግባት ዘላቂ ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላማቸው ቁርጠኛ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ሼህ ኡስማን መሐመድ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ደመረ ላቀው በበኩላቸው እንደገለጹት የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ከመንግስት ጎን ሆነው ለሰላም ያሳዩት ተነሳሽነት የሚበረታታ ነው።   የዛሬው መድረክም የሰላም እጦት በኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለማስገንዘብ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። ነጋዴው ሰርቶ ተጠቃሚ መሆን የሚችለው ሰላም በዘላቂነት ሲረጋገጥ መሆኑን ጠቅሰው፣ ህብረተሰቡ ለአካባቢው ሰላም መጠናከር ከመንግስት ጎን በመሆን የጀመረውን ተግባር እንዲያጠናክር አሳስበዋል። በደሴ እና በደብረብርሀን ከተሞች በተካሄዱ የውይይት መድረኮች የንግዱ ማህበረሰብ፣ አመራሩና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
                         
 
                       
                          በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ አቋማችን የማይናወጥ ነው -የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
                         
 
                        
                         Oct 30, 2025 279
                        
 
                         
                          ሚዛን አማን ፤ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ)፡-የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖረንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ ግን አቋማችን የማይናወጥና አንድ ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ። በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ እየጎለበተ እንዲሄድ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። በዚህም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፌዴራልና በክልሎች የጋራ ምክር ቤት በመመስረት የሀሳብ ክርክሮችን በማድረግ በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ እየሰሩ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ የሀገር ልማትና የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ዙሪያ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ኢዜአ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን አነጋግሯል። የፓርቲዎቹ አመራሮችም የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ ግን አቋማችን አንድና ሊናወጥ የማይችል ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት የሚያስቆጭና መልሳ ማግኘት እንዳለባት የጸና እምነት እንዳላቸው አንስተው በዚህ ረገድ መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴና ያለውን አቋም እናደንቃለን ብለዋል። የባህር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ የህልውና ጉዳይ ተደርጎ መያዙ ሁላችንንም የሚያስማማ በመሆኑ በሁሉም ረገድ የመንግስትን አቋም እንደግፋለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ፓርቲ ተወካይ ጎዳና ሙንኤ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ምክንያቱ የማይታወቅ፣ የሁልጊዜም ቁጭትና የታሪክ ስብራት ጭምር መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና መንግስታቸው የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን በፅኑ አምኖ ምላሽ እንዲያገኝ የጀመረውን ጥረት እናደንቃለን፤ እንደግፋለንም ብለዋል። የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ በሉአላዊነቷ እና በተለይም በባህር በር ጉዳይ ላይ አቋማችን ሊናወጥ አይችልም ሲሉም አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባልና ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አቶ ሰሎሞን መኮንን፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት ብሔራዊ ጥቅሟን በእጅጉ የጎዳ፣ የሚያስቆጭና የታሪክ ተወቃሽ የሚያደርግ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም ምክንያት እስካሁን ኢትዮጵያ ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለች መሆኑን ተናግረው መንግስት የባህር በር ሊኖራት የግድ ይላል ብሎ አቋም መያዙ ተገቢና ሁላችንም የምንደግፈው አጀንዳ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት በፍፁም የቀባይነት የሌለው መሆኑን አስታውሰው ከቀይ ባህር በቅርብ እርቀት ላይ ሆና የተቆለፈባት ሀገር ሆና መዝለቅ የለባትም ሲሉ አፅኖት ሰጥተዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በታሪክም፣ በህግም ይሁን በመልካአ ምድር የባህር በር የማግኘት መብት አላት ለዚህም ስኬት በጋራ እንቆማለን ሲሉ አረጋግጠዋል።    
                         
 
                       
                  ፖለቲካ
                 
                
                          እየተከናወነ ባለው የሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፏችንን ይበልጥ እናጠናክራለን - የባሕርዳር ወጣቶችና ሴቶች
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 72
                        
 
                         
                          ባሕር ዳር፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፡- በከተማው እየተከናወነ በሚገኘው የሰላም ግንባታና የልማት ተግባራት ላይ ተሳትፏቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የባሕርዳር ከተማ ወጣቶችና ሴቶች ተናገሩ። የከተማው ወጣቶችና ሴቶች በሰላም ማፅናት ዙሪያ ዛሬ በባሕርዳር ከተማ ተወያይተዋል። የውይይቱ ተሳታፊ ትዕግስት አባቡ በሰጠችው አስተያየት፤ መንግስት ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት በማብቃት የሚደነቅ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብላለች። የልማት ስራዎቹ የወጣቶችንና ሴቶችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ጠቅሳ፤ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አንስታለች። ለልማት ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላም ግንባታ ተሳትፎዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል ተናግራለች። ሌላው ተሳታፊ አዲሱ ዳኘው በበኩሉ፤ ከለውጡ ወዲህ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የወጣቶችና ሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ምቹ መደላደል የፈጠሩ ናቸው ብሏል። እየተከናወኑ የሚገኙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሃገሪቱን ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ደረጃ የሚያሸጋገሩ እንደሆኑም ተናግሯል። የልማት ስራዎቹ የተከናወኑት ከሰላም ግንባታ ጎን ለጎን መሆኑን ጠቅሶ፤ የልማት ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲቻል ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የበኩሉን እንደሚወጣ ገልጿል።   የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ሃላፊ ቶማስ ታምሩ፤ ከለውጡ ወዲሕ በከተማው የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተለይም ከተማዋን ለቱሪስቶችና ነዋሪዎች ምቹ በማድረግ በኩል የኮሪደር ልማት ስራው ለአብነት የሚጠቀስ ዋና ተግባር ነው ብለዋል። ሌሎች የሕዝብ ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ለዚህም የከተማው ወጣቶችና ሴቶች ድጋፍና ትብብር የጎላ መሆኑን አንስተዋል። የተጀመሩ የልማት ስራዎች የወጣቶችንና የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ተጠቃሚነት የበለጠ እንዲያሳድጉ የሰላም መፅናት ወሳኝ በመሆኑ ሴቶችና ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው አፅንኦት ሰጥተዋል።   በከተማ አስተዳደሩ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር ዓይን ገላጭ የሆኑ አበረታች የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች፣ ሕፃናትና ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ ሰብለ ዘውዱ ናቸው። ከተማዋ በተፈጥሮ ያላትን ፀጋ በኮሪደር ልማት በማጉላት ከጣና ሃይቅ ጋር ያላት ትስስር ላቅ ወዳለ ደረጃ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
                         
 
                       
                          የአካባቢያችንን ሰላም በመጠበቅ የልማት ተግባራት እንዲሳኩ የበኩላችንን እንወጣለን -ወጣቶች
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 72
                        
 
                         
                          ደሴ/ወልድያ/ ሰቆጣ፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፡- የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ የልማት ተግባራት ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚወጡ በአማራ ክልል ወጣቶች ገለጹ። "ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ወጣቶች የተሳተፉባቸው የውይይት መድረኮች በደሴ፣ ወልዲያና ሰቆጣ ከተሞች ዛሬ ተካሂደዋል። ከደሴው መድረክ ተሳታፊዎች ውስጥ ወጣት ከድር የሱፍ በሰጠው አስተያየት፤ መንግስት ሰላምን ከማፅናት ጎን ለጎን የሚያካሂዳቸው ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለወጣቶችና ለቀጣዩ ትውልድም ተስፋ የሰጡ ናቸው ብሏል። ፕሮጀክቶቹ የሀገሪቱን እድገት በማፋጠን መሰረታዊ ለወጥ የሚያመጡ መሆናቸውን ጠቅሶ፤ ከሌሎች ወጣቶች ጋር በመተባበር ሰላም በማስጠበቅ ለአካባቢው ልማት ብሎም ለሀገራዊ ፕሮጀክቶች ስኬታማነት የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ሌላዋ የመድረኩ ተሳታፊ ወጣት ቤተልሔም ፈንታው በበኩሏ፣ የማዳበሪያ፣ የጋዝ፣ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያና ሌሎች ፕሮጀክቶች መገንባት ለመጪው ትውልድ ትልቅ ተስፋ የሰነቁ ናቸው ብላለች። በዚህ ሂደት ፕሮጀክቶቹ ተሳክተው የሀገራችንን ብልጽግና ለማረጋገጥ የድርሻችንን ለመወጣት ቁርጠኛ ነን፤ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጅት ሰላማችንን ለማጽናት የጀመርነውን ስራ እናስቀጥላለን ብላለች።   የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተወካይና የሕዝብ ግንኙነት ምክትል አማካሪ አቶ አወል አህመድ በበኩላቸው፤ የከተማውን ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ ከወጣቱ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የወል ትርክትን በማስፈን ሕብረብሔራዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ወጣቶች የጀመሩትን የነቃ ተሳትፎ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።   በተመሳሳይ በወልዲያው መድረክ ከተሳተፉት መካከል ወጣት አቤል አያሌው፤ የአካባቢያቸውን ሰላም በዘላቂነት በማስጠበቅ ልማት ይበልጥ እንዲጠናከር የድርሻችንን ለመወጣት መንቀሳቀስ አለብን ብሏል። ሰላምን በማፅናት የአካባቢውና ሀገራዊ ተስፋ ሰጪ የልማት ተግባራት ከፍጻሜ እንዲደርሱ በጋራ መነሳት አለብን ያለው ደግሞ ወጣት ኃይለማሪያም ስዩም ነው። የወልድያ ከተማ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሀላፊ አቶ መላኩ ዓለሙ፤ ጽንፈኛ ቡድኑ የባዕዳን ተላላኪ በመሆን ታሪክ የማይረሳው አፍራሽ ድርጊት ለመፈፀም ቢሞክርም በፀጥታ ሀይሉ እየመከነበት በመበታተን ላይ መሆኑን አብራርተዋል። ሰላምን በዘላቂት አፅንቶ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት ወጣቶች ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።   በሌላ በኩል በሰቆጣው ውይይት የተሳተፈው ወጣት ጥላሁን አበበ፤ መንግስት ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ እያደረገ ያለው ጥረት እንደግፋለን ብሏል። ሌላው ተሳታፊ ወጣት አስፋው ገብረ መድህን በበኩሉ፤ ለሰላም መስፈን እኛም ከመንግስት ጎን ተሰልፈን የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉ ገልጿል። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጌትነት እሸቱ በበኩላቸው፤ በአካባቢ የሰፈነውን ሰላም አስጠብቆ በዘላቂነት ለማስቀጠል ወጣቶች ብሎም የፀጥታ አካላት እያደረጉት ያለው ተግባር የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገራችን ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች ላይ አተኩራለች ያሉት አቶ ጌትነት፤ በቀጣናው ያላትን ተሰሚነት ለማጠናከር ወጣቶች ሚናቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል። በከተሞቹ በተካሄደው የውይይት መድረኮች የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ ወጣቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
                         
 
                       
                          የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች ላይ በማተኮር ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል 
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 157
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች ላይ በማተኮር ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። መገናኛ ብዙኃን የሚያመነጯቸው መረጃዎች ግንዛቤን በመፍጠር፣ የሀገር ገጽታ በመገንባት፣ የዕቅድና ፖሊሲዎችን በማስተዋወቅ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ቁልፍ ሚና አላቸው። በዜጎች መካከል የሚንጸባረቁ በብዝኅነት ላይ የተመሰረቱ እሳቤዎች የሚስተናገዱበትን አጀንዳ በመቅረጽም አሰባሳቢ ትርክት ግንባታን በማስተጋባት ብሔራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ ወሳኝ መሳሪያዎች ናቸው። የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ሀገራዊ መግባባትን ለማጠናከር የመገናኛ ብዙኅን ሙያዊ ሥነ-ምግባርና ኃላፊነት ለዘላቂ ዕድገትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የዘርፉ ምሁራንም መገናኛ ብዙኅን በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን በመፍጠር የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስጠበቅ ሙያዊ ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት መምህር ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር)፤ የየትኛውም ዓለም የመገናኛ ብዙኅን የሚሰራው ለተመሰረተበት ሀገር ብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ነው ብለዋል።   በኢትዮጵያ ጉዳይ መረጃዎችን የሚያመነጩ መገናኛ ብዙኅንም ዜጎችን የሚያቀራርቡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለሀገር ዕድገት መፋጠን አቅም የሚሆኑ ዘርፎች ላይ መስራት እንደሚኖርባቸው መክረዋል። በዚህም መገናኛ ብዙኅን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስከብሩ አጀንዳዎችን በመቅረጽ ለዜጎች ሁለንተናዊ ትሥሥር በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ህዝብና መንግስትን በማቀራረብ የሀገርን የዕድገት ፖሊሲ በማስተዋወቅ የትግበራ ሂደታቸው ለዜጎች ህይወት ሁለንተናዊ ለውጥ መዋሉን ተከታትሎ የማረጋገጥ ስራ ማከናወን እንደሚጠበቅም አንስተዋል። በዜጎች መካከል ሀገራዊ መግባባትን በማጠናከር መንግስት ለብሔራዊ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት ድህነትን ለመቀነስ የሚኖራቸውን ጉልህ ፋይዳ ማሳየት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል። በተለይም የኢትዮጵያን ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ የቀይ ባሕር ባለቤትነት ብሔራዊ ጥቅም ላይ ምክንያታዊ ዘገባዎችን ማስተጋባት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። በሠመራ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ አስፈፃሚና የጋዜጠኝነት ትምህርት ክፍል መምህር መሐመድ አህመድ፤ ኢትዮጵያዊያን በብሔራዊ ጥቅምና ሀገራዊ ፍላጎቶች ላይ ልዩነት ሊኖረን አይገባም ብለዋል።   የኢትዮጵያዊያን የአንድነት አሻራ ያረፈበት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ስኬትም ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር አሰባሳቢ ትርክት መገንቢያ ግዙፍ ብሔራዊና አህጉራዊ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የብሔራዊ ጥቅም መሠረት የሆነው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም የዜጎች የጋራ ብሔራዊ አጀንዳ መሆኑን አስገንዝበዋል። በሁሉም የመገናኛ ብዙኅን አማራጮች መረጃን የሚያመነጩና የሚያሰራጩ ዜጎችም ሀገራዊ መግባባትና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ የልማት አጀንዳዎች ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ መክረዋል።
                         
 
                       
                          የባህር በር ጥያቄ የሀገር ህልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ እንሰራለን- የጋራ ምክር ቤቱ
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 104
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-የባህር በር ጥያቄን የሀገር ህልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ አድርጎ ለተግባራዊነቱ እንደሚሰራ የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን ማለታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም፤ ለጎረቤቶቻችን መናገር የምንፈልገው ኢትዮጵያ ስታደግ ለቀጣናው ልማት ምንጭ ትሆናለች፤ የምንፈልገው በትብብር ማደግ ነው፤ በመሆኑም የባህር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው በማለት አጽንኖት ሰጥተው ተናግረዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራሮች የባህር በር ጥያቄ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊ እውነታዎችን መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት የባህር በር የነበራት፣ በቀጣናው ጂኦፖለቲካዊ እንቅስቃሴም ጉልህ ተሳትፎ የነበራት ሀገር መሆኗን አስታውሰው ባለፉት 30 ዓመታት ያለባህር በር የቆየችበት ጊዜ የሚያስቆጭ መሆኑን አንስተዋል።   ባህር በር ኢትዮጵያ ከድህነት የምትወጣበት፣ በቀጣናው የዲፕሎማሲ ከፍታዋን የምታረጋግጥበት፣ ንግዷን የምታሳልጥበት ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ በምክር ቤቱ ይደግፋል ያሉት የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ ናቸው። ጉዳይ የአገር አጀንዳ እንዲሆን ላደረጉት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምስጋና እንደሚገባቸው አንስተው ጥያቄው የኢትዮጵያን ህልውና ማረጋገጫ ዋና መሳሪያ ነው ብለዋል። ሁሉም የፖለቲካ ተዋናዮችና መላው ህዝብ የባህር በር ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ በጋራ በመቆም ታሪካዊ ስራ መስራት አለበት ነው ያሉት። የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ጸሃፊ አቶ ታሪኩ ድምበሩ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ አጀንዳ ሆኖ መምጣቱ ወሳኝና መሰረታዊ ጉዳይ በመሆኑ መንግስት ሊመሰገን ይገባል ብለዋል።   የባህር በር ጥያቄው የቅንጦት ሳይሆን የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑን በማመን የምክር ቤቱ ጠቅላላ ጉባኤ የጉዳዩ አስፈላጊነትና ወቅታዊነት ላይ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ ለተግባራዊነቱ የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የባህር በር የሀገር ህልውና እና የትውልድ ጥያቄ በመሆኑ የትኛውም የፖለቲካ ተዋናይ ይህንን እውነታ እና የሀገር ብሄራዊ ጥቅም የሚዘነጋው አይሆንም ያሉት የጋራ ምክር ቤቱ ዋና ጸሃፊ ለምላሹ የጋራ ጥረታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ 22 የፖለቲካ ፓርቲዎች አባል የሆኑበት የጋራ ምክር ቤቱ የባህር በር ጥያቄን የሀገር ህልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ አድርጎ የሚወስደው እና ለምላሹም የሚሰራ መሆኑን አረጋግጧል።
                         
 
                       
                          ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) ለምክር ቤት አባላት የሰጡት ማብራሪያ የትግራይ ክልል ህዝብን የሰላምና የልማት ፍላጎት በትክክል ያመላከተ ነው- የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 140
                        
 
                         
                          መቀሌ ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለምክር ቤት አባላት የሰጡት ማብራሪያ የትግራይ ክልል ህዝብን የሰላምና የልማት ፍላጎት በትክክል ያመላከተ መሆኑን የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወቃል። በተለይም በሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ላይ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እና መንግስት ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በተመለከተ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው የትግራይ ክልል ህዝብ ፍላጎት ዘላቂ ሰላም እና የልማት ተጠቃሚነት መሆኑን ገልጸው የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ በዚህ የፌዴራል መንግስት ብዙ መስራቱን አንስተዋል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምክር ቤት አባላት የሰጡት ማብራሪያ የትግራይ ክልል ህዝብን የሰላምና የልማት ፍላጎት በትክክል ያመላከተ መሆኑን ገልጸዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል ወጣት ይልማ ሃብቴ፣ አቶ አፅበሃ አብርሃ እና መምህር ሃይለ ከለለው፤ የትግራይ ክልል ህዝብ ለግጭትና ለጦርነት የሚሰሩ አካላትን በፍጹም አይቀበልም ብለዋል።   የህዝቡ ፍላጎት ከምንም በላይ ሰላም እና ልማት መሆኑን ተናግረው ይህንን ፍላጎቱን በአግባቡ ተገንዝቦ የሚሰራለት አስተዳደር የሚሻ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የወጣቱ ፍላጎት ሰርቶ መለወጥና ህይወቱን በአግባቡ መምራት መሆኑን የተናገረው ወጣት ይልማ፤ በክልሉ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቋል። የትግራይ ክልል ህዝብ ፍላጎት ሰላሙን በመጠበቅ ለሀገር ልማት በጋራ መስራትና መጠቀም በመሆኑ ለተግባራዊነቱ የድርሻችንን ለመወጣት እንሰራለን ብሏል። በመቀለ የዓዲሐ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር ሃይለ ከለለው በበኩላቸው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለልማት ስኬት እና ለሰላም ግንባታ እያደረጉት ያለው ቀናኢነት የሚደነቅ ነው ብለዋል።   የትግራይ ክልል ህዝብም የሚሻው ይህንኑ መሆኑን ያነሱት መምህሩ የህዝቡን ፍላጎት በተረዳ መልኩ ለምክር ቤቱ የሰጡት ማብራሪያ ተገቢና ትክክለኛ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ አፅበሃ አብርሃ፤ በሁሉም መልኩ የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግ መንግስት እያከናወናቸው ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ትልቅ ተስፋ የተሰነቀባቸው መሆኑን ተናግረዋል።   በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች ሰላምን በማጽናት ልማትን በማስቀጠል የጋራ ልማትና ተጠቃሚነታችንን እውን ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል። ከትግራይ ክልል ጋር በተገናኘ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡት ማብራሪያም የክልሉን ህዝብ የሰላምና የልማት ፍላጎት መሰረት ያደረገ እና ትክክለኛ ምልከታ መሆኑን ተናግረዋል።
                         
 
                       
                           የባሕር በር ጉዳይ ምላሽ ማግኘት ያለበት የጋራ ጥያቄያችን ነው- የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 116
                        
 
                         
                          ባሕር ዳር፤ ጥቅምት 21 /2018(ኢዜአ)፡ - የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ህልውና እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ ማግኘት ያለበት የጋራ ጥያቄያችን ነው ሲል የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ። የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሀይል ንቅናቄ (አዴሀን) ሊቀመንበር ተስፋሁን አለምነህ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ህልውና እና የብሄራዊ ጥቅም ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ ማግኘት ያለበት የጋራ ጥያቄያችን ነው ብለዋል። የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርም በሀገር ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ የተለየ አቋም የሌላቸው መሆኑን አንስተው በዚህ ረገድ መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴና የያዘውን አቋም እናደንቃለን እንደግፋለንም ሲሉ አረጋግጠዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ ምክር ቤቱ በቅርበት እንደሚሰራ እና ህብረ ብሄራዊ አንድነቷና ብሔራዊ ጥቅሟ የተከበረች ሀገር ለልጆቻችን ለማስረከብ እንሰራለን ብለዋል። እንደፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለሰላም መስፈን፣ ለሕግ መከበርና ሌሎች የውስጥ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንደምንሰራ ሁሉ በብሔራዊ ጥቅሞችና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በጋራ መስራት ግዴታቸን ነው ብለዋል። መንግስት የባሕር በር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ ሲሰለፍ በተቃርኖ መቆም በታሪክ ተወቃሽ የሚያደርግና ለሕሊናም ሰላምን የሚነሳ መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከቀናት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ፤ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ የማይቀር ስለመሆኑ አስረግጠው መናገራቸው ይታወሳል።
                         
 
                       
                          ሰላምን በማጽናት ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እየተወጣን ነው
                         
 
                        
                         Oct 30, 2025 175
                        
 
                         
                          ደሴ/ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡-ሰላምን በማጽናት ልማትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን የደሴ እና የደብረ ብርሃን ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ገለጹ። የደሴ ከተማ አስተዳደር "ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሃሳብ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ዛሬ የውይይት መድረክ አካሂዷል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ወይዘሮ ሄለን አሰፋ እንደገለጹት፣ የከተማዋን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ከመንግስት ጎን በመሰለፍ የድርሻቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በደሴ ከተማ ሰላም መስፈኑ የንግድ ሥራቸውን ያለምንም ችግር ለማከናወንና ቤተሰባቸውን ለመምራት እንዳስቻላቸውም ገልጸዋል። የከተማዋን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው ሂደት በንቃት ከመሳተፈ ባለፈ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል የከተማዋ ልማት እንዲፋጠን የድርሻቸውን መወጣታቸውን አስረድተዋል።   ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ አህመድ ጀማል በበኩላቸው ለጤናማ የንግድ እንቅስቃሴ የሰላም ዋጋ የማይተካ ነው ብለዋል። አሁን ላይ በአካባቢው ሰላም በመስፈኑ ምርትና ሸቀጣሸቀጥ ከሌላ አካባቢ ወደ ከተማዋ በማምጣት ሥራቸውን በአግባቡ ለማከናወን መቻላቸውን ተናግረዋል። በአካባቢያቸው የሰፈነውን ሰላም በመጠበቅ የንግድ ሥራቸውንና ልማትን ለማፋጠን ቁርጠኛ መሆናቸውን የገለጹት አቶ አህመድ፣ የታጠቁ ኃይሎችም የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ህብረተሰቡን መካስ እንዳለባቸው ተናግረዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ ካሳው በበኩላቸው የንግዱ ማህበረሰብ የደሴ ከተማና አካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ከመንግስት ጋር በትብብር የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።   ወጣቶችን ስለ ሰላም ከማስተማር በተጨማሪ ገበያው እንዲረጋጋ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ ዜና በደብረ ብርሀን ከተማ የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት የከተማቸውን ሰላም በማጠናከር ልማት እንዲፋጠን ከመንግስት ጎን ሆነው የሚያደርጉትን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። የከተማዋ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት በዘላቂ ሰላምና በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ከከተማው መስተዳድር ኃላፊዎች ጋር ዛሬ መክረዋል።   ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ንጉሴ ማሞ ሰላም ለሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ለከተማቸው ሰላም መጠናከር የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። የንግድ ስራቸውን ለማከናወንም ሆነ ከልማት ሥራዎች ተጠቃሚ ለመሆን ሰላም ወሳኝ መሆኑን እና በከተማቸው የሰፈነውን ሰላም ለማስቀጠል የህዝብ ትብብር አስፈላጊ ነው ብለዋል። የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻልና የልማት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ሰላምን ማጽናት አይነተኛ ሚና እንዳለው የገለጹት ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ ደግሞ አቶ ሳሙኤል አውግቸው ናቸው። የሰላም እጦት ያለውን ተጽዕኖ እናውቀዋለን ያሉት ነዋሪው፣ ለሸቀጦች ዋጋ መናርና መጥፋት አንድ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል።   የንግድ ሥራቸውን በተረጋጋ ሁኔታ ለማከናወንና ሁለንተናዊ ልማት እንዲፋጠን በከተማቸው የሰፈነውን ሰላም ለማጽናት ተግተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ለእዚህም እንደ ንግዱ ማህበረሰብ አባል ከመንግስት ጎን በመቆም የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። በተለይ ስለሰላም አስፈላጊነትና ሰርቶ ለመለወጥ ሰላም ያለውን ፋይዳ ለህብረተሰቡ የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። መንግስት የጀመራቸው የልማት ስራዎች ዳር እንዲደርሱና በሰላም ወጥቶ ለመግባት ዘላቂ ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ለሰላማቸው ቁርጠኛ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ሼህ ኡስማን መሐመድ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ደመረ ላቀው በበኩላቸው እንደገለጹት የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ከመንግስት ጎን ሆነው ለሰላም ያሳዩት ተነሳሽነት የሚበረታታ ነው።   የዛሬው መድረክም የሰላም እጦት በኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለማስገንዘብ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። ነጋዴው ሰርቶ ተጠቃሚ መሆን የሚችለው ሰላም በዘላቂነት ሲረጋገጥ መሆኑን ጠቅሰው፣ ህብረተሰቡ ለአካባቢው ሰላም መጠናከር ከመንግስት ጎን በመሆን የጀመረውን ተግባር እንዲያጠናክር አሳስበዋል። በደሴ እና በደብረብርሀን ከተሞች በተካሄዱ የውይይት መድረኮች የንግዱ ማህበረሰብ፣ አመራሩና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
                         
 
                       
                          በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ አቋማችን የማይናወጥ ነው -የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
                         
 
                        
                         Oct 30, 2025 279
                        
 
                         
                          ሚዛን አማን ፤ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ)፡-የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖረንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ ግን አቋማችን የማይናወጥና አንድ ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ። በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ እየጎለበተ እንዲሄድ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። በዚህም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፌዴራልና በክልሎች የጋራ ምክር ቤት በመመስረት የሀሳብ ክርክሮችን በማድረግ በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ እየሰሩ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ የሀገር ልማትና የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ዙሪያ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ኢዜአ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን አነጋግሯል። የፓርቲዎቹ አመራሮችም የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ላይ ግን አቋማችን አንድና ሊናወጥ የማይችል ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት የሚያስቆጭና መልሳ ማግኘት እንዳለባት የጸና እምነት እንዳላቸው አንስተው በዚህ ረገድ መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴና ያለውን አቋም እናደንቃለን ብለዋል። የባህር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ የህልውና ጉዳይ ተደርጎ መያዙ ሁላችንንም የሚያስማማ በመሆኑ በሁሉም ረገድ የመንግስትን አቋም እንደግፋለን ሲሉም አረጋግጠዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ፓርቲ ተወካይ ጎዳና ሙንኤ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ምክንያቱ የማይታወቅ፣ የሁልጊዜም ቁጭትና የታሪክ ስብራት ጭምር መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና መንግስታቸው የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን በፅኑ አምኖ ምላሽ እንዲያገኝ የጀመረውን ጥረት እናደንቃለን፤ እንደግፋለንም ብለዋል። የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ቢኖርንም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም፣ በሉአላዊነቷ እና በተለይም በባህር በር ጉዳይ ላይ አቋማችን ሊናወጥ አይችልም ሲሉም አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ አባልና ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አቶ ሰሎሞን መኮንን፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት ብሔራዊ ጥቅሟን በእጅጉ የጎዳ፣ የሚያስቆጭና የታሪክ ተወቃሽ የሚያደርግ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም ምክንያት እስካሁን ኢትዮጵያ ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለች መሆኑን ተናግረው መንግስት የባህር በር ሊኖራት የግድ ይላል ብሎ አቋም መያዙ ተገቢና ሁላችንም የምንደግፈው አጀንዳ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት በፍፁም የቀባይነት የሌለው መሆኑን አስታውሰው ከቀይ ባህር በቅርብ እርቀት ላይ ሆና የተቆለፈባት ሀገር ሆና መዝለቅ የለባትም ሲሉ አፅኖት ሰጥተዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በታሪክም፣ በህግም ይሁን በመልካአ ምድር የባህር በር የማግኘት መብት አላት ለዚህም ስኬት በጋራ እንቆማለን ሲሉ አረጋግጠዋል።    
                         
 
                       
                     ማህበራዊ
                    
                   
                             አስተማማኝ እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ የኃይማኖት ተቋማት እየተወጡ ያለውን ሚና ማጠናከር ወሳኝ ነው 
                            
 
                           
                            Oct 31, 2025 86
                           
 
                            
                             አርባ ምንጭ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-አስተማማኝና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የኃይማኖት ተቋማት እየተወጡ ያለውን ሚና ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀኃፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ገለጹ። የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት ህብረት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው ጉባኤ ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ዛሬ በአርባ ምንጭ ከተማ መክሯል።   በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ቀሲስ ታጋይ ታደለ፤ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የሃይማኖት ተቋማት ሚና መጠናከር ወሳኝ ነው ብለዋል። ''ያለ ሰላም መኖር አንችልም ሰላም ለሰው ልጆች የመጀመሪያውና ተቀዳሚ የህልውና አጀንዳ ነው'' ሲሉም ተናግረዋል። ሀገር አቀፍ ኹነቱ የሃይማኖት ተቋማቱ ለሰላም፣ ለልማት እና ለአንድነት እንዲሁም ለሰላም እሴቶች መፅናት እያደረጉት ያለው ተግባር እንዲጎለብት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትልና የሰላም እሴት ግንባታና ብዝሃነት አያያዝ ዘርፍ ኃላፊ አቶ በቀለ ሎኮርማ በበኩላቸው ክልሉን የሰላም ተምሳሌት ለማድረግ የተቀናጀ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።   ክልሉ ይህን ጉባኤ ለማስተናገድ በመመረጡ መደሰታቸውን ጠቅሰው ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ ተወካይና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ መስከረም ዛፉ ፤በከተማዋ የሚካሄደው 5ኛው ሀገር አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተሳካ እንዲሆን ከህዝብ ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።   የአርባ ምንጭ ከተማ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ገበየሁ ፃራ በበኩላቸው ሰላም ለሁሉም መሠረት በመሆኑ በአካባቢው ያለው የሰላም ፀጋ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።   በጉባኤውም ሀገር አቀፍ የሃይማኖት መሪዎች፣ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚገኙ ሲሆን እንግዶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ ሲደረጉ የነበሩ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውንም አስታውቀዋል። በኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት ህብረት የሚዘጋጀው 5ኛው ሀገር አቀፍ ጉባኤ በመጪው ህዳር ወር በአርባ ምንጭ ከተማ ይካሄዳል።
                            
 
                          
                             በጂንካ ከተማ የኮሪደር ልማት የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ አስችሏል
                            
 
                           
                            Oct 31, 2025 79
                           
 
                            
                             ጂንካ ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በጂንካ ከተማ የተገነባው የኮሪደር ልማት የተሻለ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር በማድረግ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ማስቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስና ነዋሪዎች ገለጹ። በኮሪደር ልማቱ የእግረኛ መንገድ ከተሽከርካሪ መተላለፊያ መለየቱ ቀደም ሲል በሰዎች ላይ ይደርስ የነበረውን የተሽከርካሪ አደጋ ለመቀነስ ማስቻሉም ተመላክቷል።   ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የጂንካ ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት የትራፊክ አደጋ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ቡድን መሪ ኢንስፔክተር ባማዮ ይክላ፣ የኮሪደር ልማት ሥራው ከመጀመሩ በፊት እግረኞች ከተሽከርካሪዎች ጋር እየተገፋፉ ይጓዙ ነበር። በዚህም ምክንያት በተደጋጋሚ የተሽከርካሪ አደጋ ሲከሰት እንደነበር አስታውሰው፤ በተለይ ሕፃናት፣ አዛውንቶች እና አካል ጉዳተኞች ይበልጥ ሲጎዱ እንደነበር ገልጸዋል።   በከተማው የኮሪደር ልማት መገንባቱን ተከትሎ የእግረኛ እና የተሽከርካሪ መንገድ ተለይቶ መሰራቱ የትራፊክ እንቅስቃሴው ጤናማና የተሳለጠ እንዲሆን ማስቻሉን ተናግረዋል። ይህም ቀደም ሲል በተደጋጋሚ ሲያጋጥም የነበረን የተሽከርካሪ አደጋ ለመከላከል አስችሏል ያሉት ኢንስፔክተር ባማዮ፣ ለዚህም ላለፉት 90 ቀናት በከተማው ምንም አይነት የትራፊክ አደጋ እንዳልተከሰተ በማሳያነት ጠቅሰዋል። የኮሪደር ልማቱ የአደጋ ስጋት እና የትራፊክ ፖሊሶችን የሥራ ጫና እንዲቀንስ ማድረጉንም ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት የከተማው ነዋሪዎች መካከል ጀማል ኡመር እንዳሉት፣ በከተማው የተገነባው የኮሪደር ልማት እግረኞች እና ተሽከርካሪዎች በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።   ቀደም ሲል "ለተሽከርካሪ አደጋ እንጋለጥ ይሆን" በሚል ስጋት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት ህጻናት፣ አዛውንቶችና አካል ጉዳተኞች ያለስጋት በነጻነት መንቀሳቀስ የሚችሉበት ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል። የኮሪደር ልማቱ ለከተማው እድገትና ውበት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የገለጹት የከተማው ነዋሪ መሰለ ወንድሙ በበኩላቸው የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ በመንገድ ዳርቻዎች አረንጓዴና የመዝናኛ ስፍራዎች መገንባታቸውን ተናግረዋል ።   የከተማዋ ነዋሪዎች በእግር ተንቀሳቅሰው ጉዳያቸውን ማከናወን የሚችሉበትና በዚያውም ጤናቸውን የሚጠብቁበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም ጠቁመዋል። በተለይ መንገዱ ለዐይነ ስውራን ልዩ ምልክት ያለው መሆኑ የኮሪደር ልማቱን አካታችና ምቹ አድርጎታል ያሉት ነዋሪው፣ ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በከተማ አስተዳደሩ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የመሰረተ-ልማት ማስፋፊያ ፕሮግራም ቡድን መሪ አቶ ፈለቀ ወርቁ በከተማው በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።   በመጀመሪያው ምዕራፍ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከ2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት በቅቷል ብለዋል። የኮሪደር ልማቱ የእግረኛ መንገድ፣ የመዝናኛ ፓርክ፣ የመንገድ አካፋይና ዳርቻ መብራቶችን ጨምሮ መከናወኑንም አስረድተዋል። በሁለተኛው ምዕራፍ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በተለያዩ የከተማው አካባቢዎች ከስድስት ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ሥራ እንደሚተገበርም አስታውቀዋል። ለዚህም የወሰን ማስከበር ሥራዎች መጠናቀቃቸውን የጠቀሱት አቶ ፈለቀ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለማዘመን፣ ዕድገቷን ለማፋጠንና ተወዳዳሪነቷን ለመጨመር እያገዘ መሆኑ ተናግረዋል።
                            
 
                          
                             የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የቤት ባለቤት አድርጎናል
                            
 
                           
                            Oct 31, 2025 249
                           
 
                            
                             አሶሳ፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፦ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያለባቸውን የኢኮኖሚ ችግር በማቃለል የቤት ባለቤት እንዲሆኑ እንዳገዛቸው በአሶሳ ከተማ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናገሩ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የክረምት ወራትና የበጋ ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተለመደ ከመምጣቱ ባለፈ የብዙዎችን ችግር እያቃለለ ይገኛል። በአሶሳ ከተማ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል የወረዳ ሁለት ነዋሪዋ ወይዘሮ በሂዳ አብዱልባጊ ከዚህ በፊት የነበረው የመኖሪያ ቤታቸው ያረጀ በመሆኑ በክረምት እና በበጋ ወቅት ከባድ ጊዜን እንዲያሳልፉ የሚያደርግ እንደነበር ያስታውሳሉ።   ይህም ጤናቸው እንዲታወክ እና ለተለያዩ በሽታዎች እንዲጋለጡ ያደርጋቸው እንደነበር ገልጸዋል። አሁን ግን የክልሉ መንግስት ተቋማት በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች የቤት ግንባታ እና እድሳት በማከናወናቸው ቤታቸው በአዲስ መልክ ተገንብቶ ለኑሮ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው በደስታ ስሜት ተናግረዋል። " በአጭር ጊዜ ይህንን ቤት ይገነቡልኛል ብዬ አላሰብኩም ነበር" የሚሉት ወይዘሮ በሂዳ ቃላቸውን አክብረው በአጭር ጊዜ ውስጥ የቤት ባለቤት አድርገውኛል ብለዋል። መንግስት ለአቅመ ደካሞች የሚያደርገው ዕገዛ የሚያስመሰግን እና ሊጠናከር ይገባል ነው ያሉት።   አራት ልጆችን ብቻቸውን እያሳደጉ የሚገኙት የወረዳው ነዋሪ ወይዘሮ ሱጉ ሳሚ የተገነባላቸው ቤት ከብዙ ስቃይ እና መከራ እንደታደጋቸው ጠቁመዋል።   "ከዚህ በፊት ቤት ለመስራት አቅም ስላልነበረን ብዙ ፈተና አሳልፈናል" የሚሉት ወይዘሮ ሱጉ የተገነባላቸው ቤት ለሁሉም ነገር ምቹ ነው ብለዋል። በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት 210 አዳዲስ ቤቶች እና 341 ዕድሳት የተደረገላቸው ቤቶችን ለነዋሪዎች ማስረከብ መቻሉን የተናገሩት ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ገለታ ሀይሉ ናቸው።   የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በየዓመቱ እየተጠናከረ መምጣቱን የተናገሩት አቶ ገለታ በዘንድሮው ዓመት የክልሉ የመንግሥት ተቋማት የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ ላይ በተጠናከረ ሁኔታ መሳተፋቸውን ገልጸዋል። በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በክልሉ የመንግስት ተቋማት ብቻ 108 ቤቶችን ዕድሳት እና ግንባታ ለማከናወን ታቅዶ እስካሁን ከ70 በላይ ቤቶች ተጠናቀው ለተጠቃሚዎች መተላለፋቸውን ጠቁመዋል ።
                            
 
                          
                             ዜጎች ወደ ውጭ ሀገር ለሥራ እንልካለን ከሚሉ አጭበርባሪዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ
                            
 
                           
                            Oct 31, 2025 114
                           
 
                            
                             አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- ሕጋዊ መሠረትም ሆነ ከውጭ ሀገራት ጋር ውል ሳይኖራቸው ‘ወደ ውጭ ሀገራት የሥራ ስምሪት እንሰጣለን’ እያሉ በሚያጭበረብሩ አካላት እንዳይታለል ዜጎች ራሳቸውን መጠበቅ እንደሚገባቸው ተገለጸ። የውጭ ሀገራት ሥራ ስምሪት የሚሰጠው በሥራና ክኅሎት ሚኒስቴር አማካኝነት ብቻ መሆኑም ተገልጿል። በዚህም መሠረት ዜጎች ካሉበት ሆነው ለውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት መመዝገብ የሚችሉበት የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት https://lmis.gov.et/ ተዘርግቶ እየተሠራ መሆኑ ተጠቁሟል። ይህን ተከትሎም ኢትዮጵያ ስምምነት ወደ ፈረመችባቸው ሥድስት የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት ለመሄድ የሚስችሉ ስልጠናዎችና ምዘናዎች ከተከናወኑ በኋላ ስምሪቱ እንደሚሰጥ ተመላክቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከመንግሥት ዕውቅናና ፈቃድ ውጭ ወደ ውጭ ሀገራት የሚደረግ የሥራ ስምሪት አለመኖሩን በመገንዘብ፤ ዜጎች ሕይወታቸውን፣ ጊዜያቸውን ብሎም ገንዘባቸው ከማጣት እንዲቆጠብ ተጠይቋል። በሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ ደላላዎች የሚደረግ የውጭ ሀገር ጉዞ የራስን ብሎም የቤተሰብን ኑሮ ለከፋ ችግር እንደሚያጋልጥ ተገንዝቦ ከዚህ አደገኛ አካሄድ እንዲቆጠብ መክረዋል። የሥራና ክኅሎት ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አበበ ዓለሙ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሀገር ውስጥ ያሉ ፀጋዎችን መሠረት ያደረገ የሥራ ዕድል ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተሠራ ነው ብለዋል። የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ካስፈለገም በሚኒስቴሩ አማካኝነት በተዘረጉ አሠራሮች በየወረዳቸው በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎች በመሰልጠን ደኅንነታቸው ብሎም ተጠቀሚነታቸው ተጠብቆ ስምሪቱን የሚያገኙበት ሁኔታ እንዳለ አስረድተዋል። ከውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ጋር በተያያዘ መረጃዎችን ለማግኘት በ9138 ነጻ የስልክ መስመር መደወል እንደሚቻልም አመላክተዋል።
                            
 
                          
                     ኢኮኖሚ
                    
                   
                             ኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ዓለም አቀፋዊ ህጎችን ተከትላ በሰላማዊ መንገድ ወደ ቀይ ባህር እንድትመለስ እንሰራለን - የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት
                            
 
                           
                            Oct 31, 2025 100
                           
 
                            
                             አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ዓለም አቀፋዊ ህጎችን ተከትላ በሰላማዊ መንገድ ዳግም ወደ ቀይ ባህር እንድትመለስ አበክረን እንሰራለን ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡ በዓለም ላይ ከባህር በር በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆና ወደብ የሌላት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ መሆኗን በመግለጽ፤ ምክር ቤቱ ታሪካዊና ህጋዊ ጥያቄዋ ምላሽ እንዲያገኝ ሚናውን እንደሚወጣ ነው የገለፁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ እንደገለጹት፤ የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና የአካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ፤ ቀይ ባህር ኢትዮጵያ ፍትሕ ያጣችበት አጋጣሚ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ የባህር በር የኢትዮጵያ ህዝብ የተቀማ ሀብቱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሳትፈለግ ያጣችውን የባህር በር በድርድርና በሰላማዊ መንገድ እንዲመለስላት ፍትሐዊ ጥያቄ አቅርባለች ቀና ምላሽ ይገባታል ብለዋል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ኮሚቴ አባል አብርሃም በርታ (ዶ/ር) በዓለም ላይ ከባህር በር በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆና ወደብ የሌላት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ መሆኗን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ዓለም አቀፋዊ ህጎችን ተከትላ በሰላማዊ መንገድ ዳግም ወደ ቀይ ባህር መመለስ ይገባታል ብለዋል፡፡ በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ መነሻ በማድረግ የውጭ ግንኙነቶችን እንደሚወስን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ህጋዊና ታሪካዊ ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ እንዲያገኙ አስፈላጊ አዋጆችን በማጽደቅ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ድምጽ በማሰማትና የጋራ ውሳኔ በማስተላለፈ ለተፈጻሚነቱ አበክሮ ይሰራል ብለዋል፡፡
                            
 
                          
                             የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች ለወጣቶች ሰፊ የስራ ዕድልን በመፍጠር ተጠቃሚነታችንን የሚያሳድጉ ናቸው- ወጣቶች
                            
 
                           
                            Oct 31, 2025 61
                           
 
                            
                             ጎንደር/ ገንዳ ውሃ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የወጠነቻቸው የልማት ፕሮጀክቶች ለወጣቶች ሰፊ የስራ ዕድልን በመፍጠር ተጠቃሚነታችንን የሚያሳድጉ ናቸው ሲሉ የጎንደርና ገንዳ ውሃ ከተሞች ወጣቶች ገለጹ። የጎንደርና የገንዳ ውሃ ከተሞች ወጣቶች በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄደዋል፡፡ በጎንደር ከተማ በተካሄደው መድረክ የተሳተፈው ወጣት ደሴ ማለደ እንደገለጸው በአገራችን ሊካሄዱ የታቀዱ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ወጣቶች በሀገራቸው ሰርተው እንዲለወጡ የሚጨበጥ ተስፋን የሚሰጡ ናቸው።፡ በቅርቡ ይፋ የተደረጉት የጋዝ ማምረቻና የነዳጅ ማጣሪያ፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የአውሮፕላን ማረፊያና ሌሎች ፕሮጀክቶች ለወጣቱ ሰፊ የስራ ዕድልን በማመቻቸት ለፕሮጀክቶቹ ስኬት የተለየ አበርክቶ እንዲኖረው ያደርጋሉ ብሏል።   የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪው ወጣት ጀማል መሃመድ በበኩሉ በሀገራችን የተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች እንዲሳኩ እኛ ወጣቶች ሰላማችንን በመጠበቅና አንድነታችንን በማጠናከር በህብረት እንሰራለን ሲል ተናግሯል። መንግስት ለግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የሰጠው ትኩረት ወጣቱ ሰፊ የስራ እድል አንዲያገኝ ምቹ መደላድልን የሚፈጥር በመሆኑ የአካባቢያችንን ሰላም በማዝለቅ ፕሮጀክቶቹ እውን እንዲሆኑ እንሰራለን ብሏል። የሰላምና ልማት መረጋገጥ በቀጥታ የወጣቱን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው ያለው ደግሞ ሌላው የከተማው ወጣት አስማረ ማለደ ነው። በዚህም መንግስት ሰላምና ልማትን በማረጋገጥ የአገራችን እድገት ለማፋጠን በሚያደርገው ጥረት በንቃት በመሳተፍ የራሱንና የሌሎች ወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማስፋት እንደሚሰራም ተናግሯል። ወጣት ኤርሚያስ አቡሃይ በበኩሉ "እኛ ወጣቶች የሀገራችንን እድገትና ብልፅግና በማረጋገጥ ያለንን ህልምና ተስፋ ለማሳካት መስራት ይጠበቅብናል ብሏል፡፡ ሌላኛዋ የመድረኩ ተሳታፊ ወጣት ሙሉ ተገኘ በበኩሏ ፅንፈኝነትን በማውገዝና በመታገል በአካባቢው የተጀመሩ የልማትና የህግ ማስከበር ተግባራት እንዲሳኩ ኃላፊነቷን እንደምትወጣም ገልፃለች።   የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተወካይ አቶ ነጻነት መንግስቴ እንደገለጹት የኢትዮጵያን ማደግና መለወጥ የማይሹ የውስጥና የውጪ ሃይሎች የሚፈጥሩትን ሴራ በማክሸፍ ወጣቱ ታሪካዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡ የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለወጣቱ ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ጠቁመው ለስኬታቸው የጋራ ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል። የገንዳውሃ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች፣ ባህልና ስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኪሩቤል መንግስቴ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለውን አንፀባራቂ የልማት ድሎችን ለማስቀጠል የወጣቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነው። ሀገራችንን ቀዳሚ እንድትሆን ለሚያደርጉ ሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ወጣቱ ትውልድ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣም አሳስበዋል። በተካሄዱት የውይይት መድረኮች ላይም የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ወጣቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።  
                            
 
                          
                             በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ አበረታች የልማት ተግባራት እንዲጠናከሩ የድርሻችንን እንወጣለን -የተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎች
                            
 
                           
                            Oct 31, 2025 66
                           
 
                            
                             ወላይታ ሶዶ/ሀዋሳ/ጂንካ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):- በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ አበረታች የልማትና የሰላም ማስከበር ተግባራት እንዲጠናከሩ የድርሻቸውን እንደሚወጡ በወላይታ ሶዶ፣ ሀዋሳና ጂንካ ከተሞች ነዋሪዎች ተናገሩ። በሀገሪቱ ወቅታዊ የልማትና ሰላም ግንባታ ዙሪያ ኢዜአ በየከተሞቹ ነዋሪዎችን አነጋግራል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ አቶ ነጋ አንጎሬ፤ እንደ ሀገር እየተካሄዱ ያሉ የልማትና የሰላም ግንባታ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም ተጀምረው የማይጠናቀቁ የልማት ስራዎች የመልካም አስተዳደር ችግር ሆነው የቆዩትን ከለውጡ ወዲህ በመሻሻል መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት መቻሉን አንሰተዋል። ይህም ነባር ፕሮጀክቶችን ከማጠናቀቅ ጎን ለጎን በአዲስ አስተሳሰብ የሚጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት እየተጠናቀቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። እንደ ሀገር አሁን ላይ በሰላም ግንባታና በልማት መስክ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ለትውልድ የሚተላለፉ በመሆናቸው ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚውጡ ተናግረዋል። በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞችም ሆነ ገጠር አካባቢዎች እየታየ ያለው የልማት እንቅስቃሴ የተሻለች ኢትዮጵያን እንድናይ መሰረት እየጣለ ነው ያሉት ደግሞ ሌላው የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ አቶ ከበደ ኤሌ ናቸው። ለዚህም የኮርደር ልማት፣ የወንዝ ዳር ልማትና አረንጓዴ አሻራን ለአብነት ጠቅሰዋል። ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት ነው ያሉት አቶ ከበደ፤ መንግስት በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም ሰፍኖ ልማት እንዲፋጠን እያከናወናቸው ያሉት ውጤታማ ተግባራት የሚያኮሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ተካልኝ አባ እንዳሉት፤ መንግስት ለሰላም ግንባታና ለልማት በሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ ነው። በከተሞች እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ብቻ ሳይሆን የሀገር ገጽታን የቀየረና የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያሳለጠ መሆኑን ጠቅሰዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ፣ እንደሀገር ግንባታቸው የተጀመሩ የማዳበሪያ ፋብሪካ ጨምሮ ግዙፍ ፕሮጀክቶች በሀገር ኢኮኖሚ እድገት ላይ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አመልክተዋል ። እንደሀገር የተጀመሩ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ የሚያሳዩ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ ሌላዋ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሙዳይ ደመቀ ናቸው። ሀገራዊ የልማት ስራዎች የዜጎችን በሀገር ሰርቶ የመለወጥ እድል ያሰፉና ትውልድን የሚየሻገሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የጂንካ ከተማ ነዋሪ አቶ ዳኜ ዮሴፍም፤ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። የባሕር በርን ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝና ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች እንዲሳኩ ከመንግስት ጎን በመሆን የድርሻዬን እወጣለሁ ያሉት ደግሞ የከተማው ነዋሪ አቶ ጋሻው ገላው ናቸው።
                            
 
                          
                             የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ መልክአ ምድርን፣ ታሪክን፣ ህጋዊነትንና መብትን መሰረት አድርጎ ምላሽ ማግኘት ያለበት ትክክለኛ ጥያቄ ነው
                            
 
                           
                            Oct 31, 2025 111
                           
 
                            
                             ሆሳዕና፤ ጥቅምት 21/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ መልክአ ምድርን፣ ታሪክን፣ ህጋዊነትንና መብትን መሰረት አድርጎ ምላሽ ማግኘት ያለበት ትክክለኛ ጥያቄ መሆኑን በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለፁ፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነቷን ለማረጋገጥ መንግሥት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ መግለፃቸው ይታወሳል። በባህር በር ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ሙሉአለም ኃይለማርያም እንደገለፁት ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነቷን የማረጋገጥ ህጋዊም ሆነ ታሪካዊ መብት አላት። የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የቀጠናውን የልማት ትስስር የሚያጎለብት በመሆኑ በቀናነት ምላሽ ማግኘት እንደሚገባውም ነው የገለጹት፡፡ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ከልማት ትስስር አልፎም የቀጣናውን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ መልክአ ምድርን፣ ታሪክን፣ ህጋዊ መብትን መሰረት አድርጎ ምላሽ ማግኘት የሚያስችል ትክክለኛ ጥያቄ መሆኑንም አስረድተዋል። በዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ መምህር ጌታሁን አበራ በበኩላቸው የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት መብት ዓለም አቀፋዊ የህግ ድጋፍ እንዳለው ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በጋራ ተጠቃሚነትና አብሮ በመልማት ዲፕሎማሲያዊ መርህ መመራቱንና የበርካቶች ድጋፍ ማግኘቱንም አንስተዋል። ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ ለመንግስት ብቻ የሚተውና የአንድ ወቅት አጀንዳ ባለመሆኑ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባም ነው የመከሩት። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በዘላቂነት አስጠብቆ ለማስቀጠል በመንግሥት የሚደረጉ ጥረቶች የተተኪውን ትውልድ ተስፋ ጭምር ያገናዘበ መሆኑንም መምህሩ ተናግረዋል። የባህር በር ባለቤትነትን የማረጋገጥ ጥያቄው ከቀጠናው ሀገራት ጋር በትብብር ለማደግ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አክለዋል።
                            
 
                          
                  ሳይንስና ቴክኖሎጂ
                 
                
                          የወጣቶችን የፈጠራ ሃሳብ ወደተግባር የሚቀይር የፋይናንስ አቅርቦት አሰራር መዘርጋቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማፋጠን ጉልህ ጠቀሜታ አለው
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 82
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-የወጣቶችን የፈጠራ ሃሳብ ወደተግባር የሚቀይር የፋይናንስ አቅርቦት አሰራር መዘርጋቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማፋጠን ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተገለጸ። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማሳለጥ ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል የሚፈጠርለትን የሥራ ዕድል ከክህሎቱ የሚያገናኝ ምቹ አሰራር ሥርዓት ምኅዳር መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑ እሙን ነው። ይህም ወጣቶች ክህሎታቸውን በመጠቀም በሚፈጠርላቸው የሥራ ዕድል ለሀገር ዕድገትና ከፍታ ችግር ፈቺ ስኬቶችን እንዲያስመዘግቡ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፤ ከግማሽ በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ወጣት መሆኑ ለሀገር ዕድገትና ብልጽግና ከፍተኛ አቅም እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የልማት አቅም የሆነውን ወጣት ኃይል የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ስኬት እየተመዘገበ ቢሆንም ቀጣይነት ያላቸው ስራዎችን ማከናወን እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። የወጣቶችን በክህሎት የታገዘ ሥራ ፈጣሪነት አቅም ለማሳደግ የሚከናወኑ ተግባራትም በሁሉም መመዘኛ መሰናክሎችን ማለፍ እንደሚጠይቅ አስረድተዋል። በዚህም የለውጡ መንግስት ወጣቶች በተለያዩ መስኮች በሚፈጠርላቸው የሥራ ዕድል ለሀገር ልማትና ዕድገት የድርሻቸውን የሚወጡበትን ምቹ ምኅዳር መፍጠር እንደቻለ ገልጸዋል። በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የዜጎችን የሥራ ዕድል አማራጭ ተጠቃሚነትን ለማስፋትም የተቀረጹ የአሰራርና የሕግ ማዕቀፎች ውጤት እያስመዘገቡ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ወጣቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን ወደተግባር ለመቀየር የሚያጋጥማቸውን የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍም የወጣቶች የኢንቨስትመንት ባንክ ለማቋቋም ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የወጣቶች የኢንቨስትመንት ባንክም በኢትዮጵያ የገበያ ሥርዓት የተመዘገቡ ኢንተርፕርነሮች የሚያቀርቡት የሥራ አዋጭነት ተጠንቶ ያለምንም ማስያዣ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት መሆኑን አስታውቀዋል። የወጣቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ዕድገት እያስመዘገበ ነው ያሉት ሚኒስትሯ በተያዘው በጀት ዓመትም ለአምስት ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የምጣኔ ሃብት ምሁሩ ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር)፤ መንግስት ዜጎች የሥራ ዕድል የሚያገኙበትን ምቹ የአሰራር ምኅዳር የመፍጠር ኃላፊነት አለበት ብለዋል።   በዚህም ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ክህሎታቸውን ወደ ተግባር የሚቀይሩበትን የፋይናንስ አቅርቦት ለማሻሻል የተፈጠሩ የአሰራር ሥርዓቶች የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋት ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖራቸው ገልጸዋል። ይህም ወጣቶች የፈጠራ ሀሳባቸውን ወደ ተግባር በመቀየር ተጨማሪ የሥራ ዕድል አቅሞችን በማስፋት በሀገራዊ የኢኮኖሚ እድገት ላይ አዎንታዊ ሚና ማበርከት እንደሚያስችል አስረድተዋል። በቅርቡም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ትብብር የወጣቶች የኢንቨስትመንት ባንክ ማቋቋም የሚያስችል ሥምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።
                         
 
                       
                          በክልሉ የግብርና ምርምር ማዕከላት ግብርናን በማዘመን ለዘርፉ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ አድርገዋል - ቢሮው
                         
 
                        
                         Oct 30, 2025 113
                        
 
                         
                          ወራቤ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ምርምር ማዕከላት ግብርናን በማዘመን ለዘርፉ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል ለስርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም በዘር ብዜት፣ በምርምርና በቴክኖሎጂ ሽግግር ባከናወናቸው ተግባራት ላይ የመስክ ምልከታ ተካሂዷል። የቢሮው ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ ዓለምይርጋ ወልደስላሴ በዚህ ወቅት እንዳሉት በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ምርምር ማዕከላት ተጨማሪ አቅም እየሆኑን ነው። በግብርና ዘርፍ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በራስ አቅም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ከተረጂነት ለመወጣት እየተደረገ ባለው ጥረት ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል። በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ ዐሻራና በሌሎች የግብርና ሥራዎችም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት በማሳደግ በኩል ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ነው የጠቆሙት። ባለፈው ዓመት በክልሉ በበልግ፣ በመኸርና በበጋ መስኖ ልማት 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር ማሳ በማልማት 142 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ገልጸዋል። ለዚህም የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርጥ ዘር ብዜት፣ የተሻሻሉና በምርምር የተደገፉ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅና በማሸጋገር ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አስታውሰዋል። በዚህ ዓመትም 159 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ግብ ተጥሎ ወደ ተግባር መገባቱን ነው ምክትል ቢሮ ኃላፊው የተናገሩት። የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ያዕቆብ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ የግብርና ልማት ሥራውን የሚያግዙ ተግባራት በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የሀገራዊና ክልላዊ ኢንሼቲቮች ትግበራን በምርምርና በቴክኖሎጂ እያገዘ እንደሚገኝም ነው የገለጹት። የወራቤ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ቀድራላ ዋበላ(ዶ/ር) እንዳሉት ማዕከሉ ግብርናን ማዘመን የሚያስችል የምርምር፣ የዘር ብዜትና ቴክኖሎጂን የማስተዋወቅ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የአካባቢን ስነ ምህዳር መሰረት በማድረግ የዘር ብዜት፣ የሰብል ጥበቃና እንስሳት ዝርያ ማሻሻልን ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመስክ ምልከታው የክልሉ ግብርና ቢሮ፣ የምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ አመራሮችና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።
                         
 
                       
                          ለኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት አቅም የሚሆን የሰው ሃይል እያፈራን ነው -ኢንስቲትዩቱ
                         
 
                        
                         Oct 30, 2025 114
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡- ለኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት አቅም የሚሆን የሰው ሃይል እያፈራ እንደሚገኝ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ገለጸ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ማብራሪያቸው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ፕሮጀክቶቸ ዕውን መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያም ሀገርን ከጸጋዎቿ በማሰናሰል በብዝኅ የኢኮኖሚ ልማት ዕመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ ያስቻሉ የአሰራር ሥርዓቶች መዘርጋታቸውን አስረድተዋል። በማዕድን ዘርፍም የተፈጥሮ ጋዝ፣ ነዳጅና ሌሎች የማዕድን ጸጋዎችን በማልማት የኢትዮጵያን ዕድገት ወደተሻለ ማዕራፍ የሚያሸጋግሩ ግዙፍ ብሔራዊ ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን አብራርተዋል። የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ዕመርታ ለማስቀጠል ከዳንጎቴ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር የተጀመረው የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካም የአርሶ አደሩን የግብዓት አቅርቦት ፍላጎት እንደሚፈታ አንስተዋል። ኢትዮጵያን የአፍሪካ የአቬየሽን ኢንዱስትሪ ማዕከል የሚያደርጋት የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ፕሮጀክትን በተቀመጠለት የግንባታ ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ብሩክ ከድር (ዶ/ር)፤ በትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ንድፈ ሃሳብን ከተግባር በማዋሐድ ዕውቀትና ክህሎት የተላበሰ የሰው ሃይል እያፈሩ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ኢንስቲትዩቱ የሚያፈራው የሰው ሃይልም ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ ስኬታማነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት ከ400 በላይ ብቁ የብረታ ብረት ብየዳ ሙያተኞችን አሰልጥኖ በማሰማራት ገንቢ ሚና መወጣቱን አስረድተዋል። በቀጣይም በዕውቀትና ክህሎት መር ትምህርትና ስልጠና በተለያዩ መርሃ ግብሮች ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ስኬት አቅም የሚሆን የሰው ሃይል የማፍራት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። አዳዲስ ስልጠና መርሃ ግብሮችን በመቅረጽ ጭምር በግብርና ማቀነባበር፣ ሥነ-ውበት፣ በቆዳና ሌጦ ተያያዥ የኢንዱስትሪ መስኮችም ብቃት ያላቸው ሙያተኞችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝ አንስተዋል። በፕላስቲክ ቴክኖሎጂ፣ በተሽከርካሪ ጥገና ዘርፎችም የትምህርትና ስልጠና መርሃ ግብር በመስጠት የዘርፉን ዕድገት የሚደግፍ የሰው ሃብት እንደሚያፈሩ ገልጸዋል። በመጨረሻም በቅርቡ የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አስፈላጊ የሆኑ ሙያተኞችን ማፍራት የኢንስቲትዩቱ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢንስቲትዩቱ በዚህ ላይ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።  
                         
 
                       
                          በክህሎት ኢትዮጵያ መርሃ ግብር በቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች እየተገኙ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል
                         
 
                        
                         Oct 29, 2025 170
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ በክህሎት ኢትዮጵያ መርሃ ግብር በቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ከወጣቶች ጋር በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን የስራና ከህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የተመረቱ የተኪ ምርት ቴክኖሎጂዎች ማስተዋወቂያ ፕሮግራም እየተካሄደ ይገኛል።   ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ችግሮችን ወደ ዕድል ለመቀየር ከሚተጉ ወጣቶች ጋር የሚከናወኑ ተግባራትን በማጠናከር ኢትዮጵያን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እየተሰራ ነው። ባለፉት ሁለት ዓመታት በተካሔደው በክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም የቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ስራዎች ከወጣቶች ጋር በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች እየተገኙ ነው ብለዋል። ችግር ፈቺና በርካታ ስራዎችን ማከናወን የሚያስችሉ አማራጮች ያሏቸው ቴክኖሎጂዎች በስፋት እየተመረቱ መሆኑን ተናግረዋል።   በመሆኑም የፈጠራ ሰራዎችን ወደ ምርት ለማስገባት የግሉ ዘርፍ በስፋት እንዲሰማራም ጠይቀዋል። በዛሬው እለት በተካሔደው መርሃ ግብር ላይ የቀረቡት ቴክኖሎጂዎች በመደመር እሳቤ ክህሎትና እውቀትን በጋራ መምራት እንደሚቻል የሚያመላክቱ ናቸው ብለዋል። የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ፈጠራን ማበረታታት ፍጥነትን ማሳደግ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነን ሲሉም ገልጸዋል።   በኢንስቲትዩቱ ለመጀመሪያ ጊዜ አዳዲስ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች መመረታቸውንም ተናግረዋል። ለአብነትም ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንዳክሸን ሞተር መሰራቱን ፣ የኤሌትሪክ ተሸከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ቴክኖሎጂ ፣ ስማርት የመንገድ ዳር መብራቶች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል። በቴክኖሎጂ ማስተዋወቂያ መርሃ ግብሩ ላይ ስራዎቻቸውን ካቀረቡት መካከል በኢንስቲትዩቱ የቴክኖሎጂ ዲፓርትመንት ቴክኖሎጂ ዴስክ ሀላፊ አቶ ወጋየው ሙሉነህ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንዳክሸን ሞተር መስራቱን ገልጸው፤ ፈጠራውን ማንኛውንም ሞተር ማንቀሳቀስ የሚያስችል ለኢንዱስትሪዎች ትልቅ ጠቀሜታ ያለውና የውጭ ምንዛሬ ወጪን መቀነስ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።   በቴክኖሎጂ ፈጠራ የተሰማራው ወጣት አቤል ማሰረሻ በበኩሉ ስማርት የመንገድ ዳር መብራቶች መስራቱን ገልጾ ዘመናዊ ቴክኖሎጂው ከመብራት አገልግሎት በተጨማሪ ካሜራና ሌሎች ሴንሰሮች ያለው በመሆኑ መረጃ እንደሚሰበሰብም ጠቁሟል።          
                         
 
                       
                  ስፖርት
                 
                
                          ኢትዮጵያ የምታዘጋጀው የሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 64
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የምታዘጋጀው የሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል ዛሬ ይፋ ሆኗል። 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ በ2026 በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይከናወናል። በውድድሩ ላይ የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበራት ምክር ቤት(ሴካፋ) ዞንን ወክለው የሚሳተፉ ሁለት ሀገራት የሚለዩበት የማጣሪያ ውድድር በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ከህዳር 6 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ሴካፋ የማጣሪያ ውድድሩ የምድብ ድልድል ዛሬ በዩጋንዳ ይፋ አደርጓል። በምድብ አንድ አዘጋጇ ኢትዮጵያ ከሶማሊያ፣ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሩዋንዳ ጋር መደልደሏን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ዩጋንዳ፣ ታንዛንያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን እና ብሩንዲ በምድብ ሁለት የተደለደሉ ሀገራት ናቸው። ውድድሩ በአበበ ቢቂላ እና ድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየሞች ይካሄዳል። በማጣሪያው ለፍጻሜ የሚያልፉት ሁለት ሀገራት የሴካፋ ዞንን ወክለው ለአፍሪካ ዋንጫ ያልፋሉ። እ.አ.አ በ2026 በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇ ሞሮኮን ጨምሮ 16 ሀገራት ይሳተፋሉ።
                         
 
                       
                          መንግስት ለእግር ኳስ ስፖርት የሰጠው ትኩረት ውጤታማነትን ለማሻሻል መነሳሳትን የሚፈጥር ነው 
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 88
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-መንግስት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ የእግር ኳስ ቡድን ለመገንባት የሰጠው ትኩረት ውጤታማነትን ለማሻሻል መነሳሳት የሚፈጥር ነው ሲሉ የእግር ኳስ ስፖርት አመራሮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ማብራሪያ ካነሷቸው ጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ እግር ኳስ ይገኝበታል። በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ በተፈለገው ደረጃ አለማደጉና ብሔራዊ ቡድኑ የአፍሪካ ዋንጫ ላይ አለመሳተፉ ብዙዎችን እንደሚያስቆጭ ተናግረዋል። መንግስት ይህን ቁጭት ለመቀየር ለእግር ኳስ እድገት በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸው፤ ለአብነትም ባለፉት አመታት ከ1 ሺህ በላይ ትናንሽ ስታዲየሞች መገንባታቸውን አንስተዋል። የተገነቡት ሜዳዎች ብቁ ታዳጊዎችን ለማፍራት ትልቅ ሚና እንደሚጫቱ ገልጸው ከአስር አመት በኋላ ብቁ የእግር ኳስ ተጨዋቾች ማፍራት እንደሚቻል በማብራሪያቸው አስታውቀዋል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የእግር ኳስ ስፖርት አመራሮች መንግስት በተለይ ለእግር ኳስ የሰጠው ትኩረት ከዚህ ቀደም ያልታየና ይበልጥ የሚያነሳሳ መሆኑን ተናግረዋል። የአርሲ ነገሌ እግር ኳስ ክለብ ስራ አስኪያጅ ጌታነህ ታደሰ ፤ መንግስት ለእግር ኳስ ስፖርት እድገት ወሳኝ የሚባሉ መሰረተ ልማቶችንና ስታዲየሞችን ገንብቷል ፤ እየገነባም ይገኛል ብለዋል።   መሠረተ ልማቶቹ በተለይ ታዳጊዎችን በማፍራት ብቁና ተፎካካሪ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው ጠቅሰዋል። የባቱ እግር ኳስ ስፖርት ክለብ ፕሬዝዳንት ተስፋዬ ኤዳዎ መንግስት እግር ኳሱን ለማሳደግ የጀመረው ተግባር ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ትንሳኤ የጎላ ሚና አለው ብለዋል።   በተለይ ታዳጊዎችን መሠረት በማድረግ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችና ሌሎች ተግባራት ለእግር ኳስ እድገት ጠንካራ መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ስፖርት ክለብ ስራ አስኪያጅ ከነዓን በለጠ መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት ውጤታማ ቡድን ለመገንባት ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥር መሆኑን አስታውቀዋል፡፡   ታዳጊዎች ላይ መስራት ለእግር ኳስ እድገት ወሳኝ በመሆኑ ክለቦች ታዳጊዎችን ወደ ዋናው ቡድን ማሳደግ ላይ በትኩረት መንቀሳቀስ አለባቸው ሲሉ ተናግረዋል ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ባህሩ ጥላሁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በእግር ኳሱ ዙሪያ ያስተላለፉት መልዕክት ትልቅ ኃላፊነት እንዳለብን የሚያመላክት ነው ብለዋል።   በቀጣይ ተፎካካሪና ውጤታማ ቡድን ለመገንባት መንግስት የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ለመጠቀም ፌዴሬሽኑ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያን እግር ኳስ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም በእኔነት ስሜት በጋራ መረባረብ አለበት ሲሉ ባለሙያዎቹ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
                         
 
                       
                          ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ምድቡን መቀላቀል ሳይችል ቀርቷል
                         
 
                        
                         Oct 30, 2025 115
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ሁለተኛ ዙር ከወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒራሚድስ ጋር ዛሬ ባደረገው የመልስ ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፏል። ማምሻውን በጁን 30 ኤር ዲፌንስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሙስጠፋ ዚኮ እና ኤወርተን ዳ ሲልቫ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳረፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ፒራሚድስ በድምር ውጤት 3 ለ 1 በማሸነፍ ምድብ ድልድሉን መቀላቀል ችሏል። ክለቦቹ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ አንድ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ መድን የመጀመሪያ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው ሁለተኛ ዙር ላይ ተገቷል። ቡድኑ አምናው በታሪኩ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ማሸነፉን ተከትሎ ነው በአህጉራዊ መድረክ የመሳተፍ እድል ያገኘው። የግብጹ ፒራሚድስ ክለብ የወቅቱ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ የዋንጫ ባለቤት ነው።
                         
 
                       
                          በሊጉ ድሬዳዋ ከተማ ሲያሸንፍ  አዳማ ከተማ ከሀዲያ ሆሳዕና አቻ ተለያይተዋል 
                         
 
                        
                         Oct 30, 2025 109
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ተካሄደዋል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታን 2 ለ 1 አሸንፏል። አሰጋኸኝ ጴጥሮስ በ31ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ግብ መቀሌ 70 እንደርታ መሪ ሆኗል። መሐመድ ኑር ናስር በ49ኛው እና አቤል አሰበ በ93ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፏቸው ጎሎች ድሬዳዋ ከተማን አሸናፊ አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ በስድስት ነጥብ ደረጃውን ወደ ሰባተኛ ከፍ አድርጓል። መቀሌ 70 እንደርታ በአንድ ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል።   በተያያዘም አዳማ ከተማ ከሀዲያ ሆሳዕና በአዲስ አበባ ስታዲየም ያደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አዳማ ከተማ በሶስት ነጥብ 11ኛ፣ ሀዲያ ሆሳዕና በሁለት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ የሶስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የአራተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይካሄዳል።
                         
 
                       
                  አካባቢ ጥበቃ
                 
                
                           የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ቃል ኪዳን እና የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጉዞ 
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 64
                        
 
                         
                          ብዝኃ ህይወት ሁሉንም ሥነ-ሕይወታዊ ኃብቶች፣ እፅዋት፣ እንስሳትና ደቂቅ አካላት እንዲሁም በውስጣቸው የያዟቸው ዘረ-መሎችና እነዚህ የሚፈጥሯቸውን ውህዶች የሚያካትት ነው። የሁሉም ስርዓተ ምህዳር እና የሰው ልጆች የመኖር መሰረት ነው ብዝሃ ህይወት። እንደ አንዳንድ ጥናቶች ከሆነ በዓለማችን ካሉ ህይወት ካላቸው 8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዝርያዎች መካከል 80 በመቶዎቹ ገና ያልተገኙ ናቸው። የዓለም ብዝሃ ህይወት ቁልፍ ጠቀሜታዎች አሉት። የምግብ ምርታማነት፣ ንጹህ ውሃ እና አየር፣ ለርክበብናኝ (ፖሊኔሽን) እና አየር ንብረትን መቆጣጠርን ጨምሮ በርካታ ጠቃሜታዎች እንዳሉት የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ብዝሃ ህይወት ከ44 ትሪዮን ዶላር በላይ ወይም የዓለምን ዓመታዊ 50 በመቶ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) ይሸፍናል። የዓለም የብዝሃ ህይወት እና የስነ ምህዳር አገልግሎቶች የበይነ መንግስታት የሳይንስ ፖሊሲ መድረክ ((IPBES) በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ በሰው የተለያዩ ተግባራት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የመሬት አጠቃቀም ምክንያት አንድ ሚሊዮን ገደማ ህይወት ያላቸው ዝርያዎች ሊጠፉ እንደሚችሉ ስጋቱን አስቀምጧል። በዚህ የዓለም ቀውስ ውስጥ አፍሪካ የብዝሃ ህይወት እምቅ ሀብቶች ያላት አህጉር ሆና ተገኝታለች። የብዝሃ ህይወቱ በርካታ እና ጫና መቋቋም የሚችሉ የአይበገሬነት አቅም ያላቸው ናቸው። የዓለም አንድ አምስተኛ እጽዋት፣ አጥቢ እንስሳት እና አዕዋፋት የሚገኙት በአፍሪካ ነው። ከ50 ሺህ በላይ የእጽዋት ዝርያዎች፣ 1 ሺህ 100 አጥቢ እንስሳት፣ 2 ሺህ 500 የአዕዋፋት እና ከ3000 በላይ የአሳ ዝርያዎች ይገኛሉ። የዓለማችን ሁለተኛው ጥብቅ ደን የኮንጎ ጥቅጥቅ ደን፣ የቦትስዋና ኦካንጋቮ ዴልታ፣ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ስፍራዎች እና የማዳጋስካር ልዩ ስነ ምህዳሮችና ዝርያዎች ከአፍሪካ ዋነኛ ብዝሃ ህይወቶች መካከል ይጠቀሳሉ። የአፍሪካ ብዝሃ የኔዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ ከማሻሻል ባለፈ የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት በዘላቂነት ማስቀጠል የሚችል አቅም ያለው ነው። ይሁንና የአፍሪካ ብዝሃ ህይወቶች ለተለያዩ ፈተናዎች የተጋለጡ ናቸው። አህጉሪቷ በየዓመቱ 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር ገደማ ደን እንደምታጣ መረጃዎች ያሳያሉ። እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ህዝብ ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቀው የአፍሪካ ህዝብ፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ህገ ወጥ አደን ፣ ዘላቂነት የጎደለው የመሬት አጠቃቀም እና ብክለት የአህጉሪቷን ብዝሃ ህይወት ስርዓት እየጎዱ ይገኛሉ። የአፍሪካ ጥብቅ ስፍራዎች ለማስተዳደር በዓመት ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያስፈልግ ቢሆንም አንዳንድ ሀገራት በቂ ኢንቨስመንት እየመደቡ አይገኝም። አፍሪካ የሶስትዮሽ ተፈጥሯዊ ቀውሶችን እያስተናጋደች ትገኛለች ማለት ይችላል። የብዝሃ ህይወት መመናመን፣ ብክለት እና የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ተግዳሮቶች ናቸው። የአስተዳደር ስርዓት አለመጠናከር፣ የተገደበ የፋይናንስ አቅርቦት እና የአካባቢ ማህበረሰብ መሪዎች በውሳኔ መስጠት ውስጥ አለመሳተፋቸው በዋናነት የሚጠቀሱ ፈተናዎች እንደሆኑም ይነገራል። የአፍሪካ ሀገራት የብዝሃ ህይወት ችግሮችን ለመፍታት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛል። ከነዚህም አንዷ ኢትዮጵያ ናት። ኢትዮጵያም ከፍተኛ የብዝኃ ሕይወት ኃብት ካላቸው አገራት መካከል አንዷ ናት። አሁን ላይ አገሪቱ ከ6 ሺህ በላይ የእፅዋት ኃብቶች ያላት ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ 600 ወይም 10 በመቶ የሚሆኑት በአገሪቱ ብቻ የሚገኙ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢንስቲትዩት መረጃ ያመለክታል።   ጎን ለጎንም የወፍ ዝርያዎችን ጨምሮ በየብስና በውኃ አካላት ውስጥ የሚኖሩ የተለያዩ ዓይነት ዝርያ ያላቸው በርካታ እንስሳት በኢትዮጵያ ይገኛሉ። ይሁንና የየብስና የውኃማ አካላት አካባቢ መለወጥ ለእነዚህ ብዝኃ ሕይወት ኃብቶች ሥጋት እየሆነ መምጣቱን ነው ኢንስቲትዩቱ የገለጸው። በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለትና ዘለቄታዊ ያልሆነ የተፈጥሮ ኃብት አጠቃቀም ለብዝኃ ሕይወት ኃብቶች መመናመን ምክንያቶች ናቸው። የሕዝብ ቁጥር መጨመርን ተከትሎ ደን ወደ እርሻ መሬትነት መቀየር እንዲሁም መጤ ወራሪ አረሞች ነባር አገር በቀል ዝርያዎች የሚበቅሉበትን ሥፍራ መያዝም ሌላኛው ምክንያት ነው። ይህንንም ተከትሎ ወይራ፣ ዝግባ፣ ቀረሮ፣ ዋንዛ፣ ጥቁር እንጨትና ኮሶ እየተመናመኑ ካሉ የእፅዋት ብዝኃ ሕይወት ዝርያዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ዝርያዎቹ አንዴ ከጠፉ መልሰው የማይገኙ በመሆናቸው ኢንስቲትዩቱ ዝርያዎቹን የማራባትና የማብዛት ሥራ በልዩ ትኩረት እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል። ከእነዚህም በተጨማሪ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውና በኢትዮጵያ ብቻ ያሉ የእፅዋትና እንስሳት ብዝኃ ሕይወት ዝርያዎችን የመጠበቅ ሥራ እየተከናወነ ነው። በዚህም የቀረሮ የእጽዋት ዝርያ የማብዛት ሥራ እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች የተመናመኑ የዳልጋ ከብቶች ወደ ነበሩበት የመመለስ ሥራም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። በተመሳሳይ "የሸኮ ዳልጋ ከብት" እየተባለ የሚጠራውን ዝርያ የማብዛት እንዲሁም በጣና ኃይቅ የዓሳ ዝርያዎች ላይ ያለውን መመናመን ለመቀልበስም የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ነው ኢኒስቲትዩቱ ያስታወቀው። ጥብቅ አካባቢዎችን የማስፋት፣ የእፅዋት አፀድ ጥበቃ፣ የዘረመልና የማኅበረሰብ የዘር ባንኮችን በየአካባቢው የማስፋት ተግባርም እየተሰራ መሆኑን አመልክቷል። የአረንጓዴ አሻራ መርኃ-ግብርም የብዝኃ ሕይወትን ከመጠበቅና ከማስቀጠል አኳያ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ያሏትን የብዝኃ ሕይወት ሃብቶች የመጠበቅ ተልዕኮ የተሰጠው የኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩትም ኃብቶቹን የማንበር (የመጠበቅ)፣ ዘለቄታዊ አጠቃቀምና ፍትሃዊ የጥቅም ተጋሪነት ላይ እየሰራ ይገኛል። በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎች እና ቀጣይ እርምጃዎች የሚመክር ጉባኤ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ከጥቅምት 23 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ቃል ነው። ጉባኤው ለአፍሪካ ብዝሃ ህይወት መመናመን፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ብክለት የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ መስጠት የሚያስችል መድረክ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። የአፍሪካ ቀዳሚ የብዝሃ ህይወት አጀንዳዎች ምክክር ይደረግባቸዋል። አህጉር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ትስስርን ማጠናከር እና ለብዝሃ ህይወት ክብካቤ የፋይናንስ ሀብትን በተቀናጀ ሁኔታ ማሰባሰብ ሌሎች የጉባኤው አጀንዳዎች ናቸው። ኢትዮጵያ እና የጉባኤው አዘጋጅ ቦትስዋን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት በብዝሃ ህይወት ጥበቃ እያከናወኗቸው ያሉ ስራዎችን አስመልክቶ ልምዳቸውን ያጋራሉ። እ.አ.አ በ2026 በአርሜኒያ በሚካሄደው 17ኛው የዓለም የብዝሃ ህይወት ጉባኤ (ኮፕ 17) ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች የአፍሪካን ድምጽ በጋራ ማሰማት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ይደረጋል። ጉባኤው አንድ ብዝሃ ህይወት የልማት አቅም ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ብልጽግና አረጋጋጭ ሞተር መሆኑ ግልጽ መልዕክት የሚተላለፍበት መድረክ ነው። ፍላጎቶች ተጨባጭ እና መሬት ወደወረዱ መፍትሄዎች ማውረጃ አማራጭ ሆኖም ያገለግላል። በአርሜኒያ ለሚገሄደው ዓለም አቀፍ ጉባኤ አፍሪካ ፍትሃዊ የፋይናንስ አቅርቦት እንድታገኝ፣ ሁሉን አቀፍ የብዝሃ ህይወት አስተዳደር እንዲረጋገጥ እና ለፍትሃዊ የጥቅም ተጋሪነት ድምጿን ለማሰማት ስንቅ ለሚሆን የሚያስችል አህጉራዊ መድረክ ጭምር ነው ማለት ይቻላል። በአፍሪካ ያለውን የብዝሃ ህይወት አቅም በውጤታማ የአስተዳደር ስርዓት፣ አካታች የማህበረሰብ ተሳትፎ እና ዓለም አቀፍ ትብብር አማካኝነት ወደ ዘላቂ እድገት ምንጭነት ማሸጋገር እንደሚቻል ጥርጥር የለውም። የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ስራ ለዓለም የብዝሃ ህይወት ግቦች መሳካት ትልቅ አበርክቶ ይኖረዋል። በብዝሃ ህይወት ላይ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ለአፍሪካ መጻኢ ጊዜ መሰረት እንደመጣል ይቆጠራል።
                         
 
                       
                          የአኙዋ ባዮስፌር በዩኔስኮ መመዝገቡ ኢትዮጵያ በብዝሃ ሕይወት ጥበቃና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂዎች ስኬት እያስመዘገበች ለመሆኑ ሁነኛ ማሳያ ነው 
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 142
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-የአኙዋ ባዮስፌር በዩኔስኮ በሰውና ባዮስፌር (ማፕ) መርሃ ግብር መመዝገቡ ኢትዮጵያ በብዝሃ ሕይወት ጥበቃና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂዎች ስኬት እያስመዘገበች ለመሆኑ ሁነኛ ማሳያ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። ባዮስፌር ሪዘርቭ ሰውና ተፈጥሮን አስማምቶ ማኖር የሚያስችል የጥበቃ ስልት ነው። በጋምቤላ ክልል የሚገኘው የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ለኢትዮጵያ ስድስተኛው የባዮስፌር ሪዘርቭ በመሆን በዩኔስኮ ተመዝግቧል። ባዮስፌሩ ስድስት የተለያዩ ሥነ-ምህዳሮችን ያካተተ ሲሆን እርጥብ የአፍሮ-ሞንታኔ ደኖች፣ የሽግግር የዝናብ ደኖች፣ የወንዝ ዳር እፅዋት፣ ረግረጋማ ቦታዎች እና ዛፍ የበዛባቸው ሳቫናዎች ይገኙበታል።   የባዮስፌሩ መመዝገብ የሀገሪቱን የጥብቅ ቦታ ሽፋን የሚያሳድግና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ሥራን ለዓለም ለማጋራት የሚያስችል መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት የደንና ግጦሽ መሬት ብዝሃ ሕይወት ምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበራ ስዩም ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባዮስፌር ለተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ለሰዎች የልማት ተጠቃሚነት ሚና አለው።   ይህም ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ፣ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና ምርምርና ጥናት ለማካሄድ ሥራ ላይ ይውላል ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ሁለት ዓመታት የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭን ለማስመዝገብ ሲሠራ መቆየቱን አንስተው፤ ዘንድሮ በቻይና በተካሄደው ጉባዔ በዩኔስኮ ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል። የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭ ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር በላይ ስፋት ያለው፣ እምቅ የብዝሃ ሕይወት ሃብትና የማኅበረሰብ ተፈጥሮን የመጠበቅ ባህልን አጣምሮ የያዘ የጥበቃ ስፍራ ነው ብለዋል። የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭ መመዝገብ የሀገሪቷን ጥብቅ ቦታዎች አሁን ካለበት 12 በመቶ ወደ 30 በመቶ በማሳደግ ዓለም አቀፍ ግብ ለማሳካት እገዛ ያለው መሆኑን አቶ አበራ ተናግረዋል።   የአኙዋ ባዮስፌር መመዝገብ ኢትዮጵያ ያላትን ፀጋ ለዓለም ይዛ የቀረበችበትና ለሀገር ገጽታ ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ምቹ ፖሊሲ፣ የብዝሃ ሕይወት ሃብትና የማኅበረሰብ ዕውቀት በማቀናጀት የተፈጥሮ ሃብት በመጠበቅ ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ያስቻላትን ልምድ ለዓለም የምታካፍልበት መሆኑንም አብራርተዋል። የአኙዋ ባዮስፌር መመዝገብ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም እና ኢትዮጵያ ለያዘችው የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ጠቀሜታ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል። በተያዘው የ2018 በጀት ዓመት ሁለት ተጨማሪ ባዮስፌር ሪዘርቮችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል።   የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ በበኩላቸው፤ የአኙዋ ባዮስፌር ሪዘርቭ መመዝገብ የአገሪቱን የጥበቃ ቦታ ሽፋን የሚያሳድግ ነው ብለዋል። የአኙዋ ባዮስፌር፣ የካፋ፣ የሸካ፣ የያዩ፣ የጣና ሐይቅ እና የመጀንግ ደን ባዮስፌር ሪዘርቮችን በመቀላቀል በዩኔስኮ እውቅና ያገኘ የኢትዮጵያ ስድስተኛው ባዮስፌር ሪዘርቭ ነው።
                         
 
                       
                          ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ  ደረጃ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው
                         
 
                        
                         Oct 29, 2025 159
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚችል ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደርና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ አኒል ኩማር ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በብዝሃ የአየር ንብረት የታደለች፤ ልዩ ልዩ የተፈጥሮ ሀብቶችን የያዘች፣ በርካታ እፅዋቶችና የዱር እንስሳት ዝርያዎች የሚገኙባት መሆኗን አምባሳደሩ ተናግረዋል፡፡ አምባሳደሩ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሐብትንና አካባቢን ለመጠበቅ እያከናወነችው ያለው ተግባር በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚችል ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ የአገሪቱን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ ለብዝሃ ህይወት መጎልበት ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ስራው አስደናቂ መሆኑን ተናግረዋል። በአፋር ክልል የሚገኘው ዝቅተኛው የደናክል በረሃ እና የተለየ የአየር ንብረት ያለው የስምጥ ሸለቆ መነሻ ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ አረንጓዴ የሆኑና ከፍተኛ የዝናብ መጠን የሚያገኙ ደጋማ አካባቢዎችን የያዘች መሆኗንም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያሉ ልዩ ልዩ የአየር ንብረት ጸባዮች፣ የዕጽዋትና የዱር እንስሳት ዝርያዎች ሀገሪቱን ብዝሃ ተፈጥሮ የተቸራት አድርጓታል ብለዋል፡፡ ይህም የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስፋት ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አመላክተዋል፡፡ አምባሳደሩ በኢትዮጵያ የተተገበሩ እንደ አረንጓዴ አሻራ ያሉ መርሃ-ግብሮችና ሰፋፊ የልማት ስራዎች ለሀገሪቱ የወደፊት ብልፅግና ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው ጠቅሰው ፤ የተተከሉት ዛፎች እንዲጸድቁ የሚደረገውን እንክብካቤ አድንቀዋል። በቀጣዩች አስር ዓመታት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደማሚ ለውጦችን ታስመዘግባለች ሲሉም ገልጸዋል። ህንድ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ለምታከናውነው ተግባር አድናቆት እንዳላት ጠቁመው፤ አገራቸው በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ አስፈላጊነት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ አቋም እንዳላት ተናግረዋል፡፡ ህንድ እና ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ የጋራ ስምምነት እንዳላቸው አስታውሰው፡ ትብብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ያከናወነቻቸው ተግባራት የአዕዋፋትንና የዱር እንስሳትን ስደት ትርጉም ባለው መልኩ መቀነሱ ይታወቃል፡፡
                         
 
                       
                          በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደናቂ የልማት ስኬት ማስመዝገብ ተችሏል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
                         
 
                        
                         Oct 28, 2025 174
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡-በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስደናቂ የልማት ስኬት ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው። በመደበኛ ስብሰባው ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምላሽና ማብራሪያቸው፤ 2017 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ የታሪክ እጥፋት ውስጥ ይቻላሉ ተብሎ የማይታሰቡ ጉዳዮች የተቻሉበት የስኬት ዓመት እንደነበር ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ያነገባቸውን ዓላማዎችና ያስገኛቸውን ውጤቶች አብራርተዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአንድ ዘርፍ ላይ ተንተርሶ ከድህነት ሊወጣ አይችልም በሚል ብዝኅ ዘርፍና ብዝኃ ተዋናይ የኢኮኖሚ አቅጣጫ ላይ የተነደፈው ፖሊሲ በእጅጉ ውጤታማ እየሆነ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች ዘርፎች ሳይዘነጉ አምስቱ ግንባር ቀደም የተሰናሰሉ በብዝኅ ዘርፍ ቢመሩ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እንደሚያሻሽሉ እምነት መጣሉን አስረድተዋል። ግብርና እና ማዕድን ለኢንዱስትሪ ግብዓት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ ኢንዱስትሪውም ግብርናን የሚያፋጥን ማሽን ፈጣሪ ነው ብለዋል። ቴክኖሎጂ የታከለበት ብዝኅ ዘርፍ የኢኮኖሚ ልማትም ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ያስቻለ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ እንደሚገኝ አንስተዋል። የብዝኅ ተዋናይነትም መንግስት አንድ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ በመሆን ከግሉ ዘርፍ፣ ከህዝብና የልማት አጋሮች ጋር ተሳስሮ የኢትዮጵያን ልማት በየፈርጁ ማፋጠን አለበት የሚል እምነት መያዙን ገልጸዋል። የግልና መንግስት አጋርነት እሳቤ ያለ ቢሆንም የመንግስትና ህዝብ አጋርነት ግን ግልጽ አቅጣጫ የተቀመጠለት ከለውጡ በኋላ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም በመንግስት የህዝብ አጋርነት ኢትዮጵያ በርካታ ስኬቶች ማስመዝገቧን ጠቅሰው፤ ለዚህም የአረንጓዴ አሻራ 48 ቢሊየን ችግኞች ስኬት ማሳያ ነው ብለዋል። እያንዳንዱ ችግኝ ከጅምሩ እስከ ተከላ መርሃ ግብሩ ባለው ሂደት አንድ ዶላር ቢወስድ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ 48 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስት ማድረግ መቻሏን አስረድተዋል። በዚህም ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ያለመታከት ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን በመስጠት በየዓመቱ ስለሰሩ ይህን ያክል ሃብት ያስወጣ የነበረን ስራ በመንግስትና በህዝብ የተቀናጀ ትብብር ማሳካት ተችሏል ብለዋል። በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ የሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
                         
 
                       
                  ዓለም አቀፍ ዜናዎች
                 
                
                          በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 68
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል።   ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል።   ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
                         
 
                       
                          የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
                         
 
                        
                         Oct 31, 2025 112
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
                         
 
                       
                          ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው  
                         
 
                        
                         Oct 24, 2025 383
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡   በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡   ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡   በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
                         
 
                       
                          የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀመረ
                         
 
                        
                         Oct 24, 2025 265
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፦11ኛው የጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ከዛሬ ጥቅምት 14 እስከ 16/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው 11ኛው ጣና ፎረም በባሕር ዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት፣የዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጣና ፎረም "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሃሳብ በባሕር ዳርና አዲስ አበባ ከተሞች በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የሚመክር ይሆናል። የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ተሳታፊ ሙያተኞች በአፍሪካ የደኅንነት ጉዳዮችና በአፍሪካዊ መፍትሔዎች ልምድና ዕውቀታቸውን የሚያካፍሉበት ዝግጅትም ተጠባቂ የፎረሙ የመርሃ ግብር አካል ነው። በፎረሙ ላይ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች ምክክር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
                         
 
                       
                  ሐተታዎች
                 
                
                          የብዙዎች ቤት…
                         
 
                        
                         Oct 27, 2025 267
                        
 
                         
                          እስካሁን በተደረገ የጥናት ውጤት መሠረት ከ81 በላይ የአጥቢ እንስሣት፣ ከ450 በላይ የአዕዋፍ እና ከ400 በላይ የእፅዋት ዝርያዎች መኖሪያ ነው። ከእነዚህ መካከል አምስቱ የአዕዋፍ ዝርያዎች በዚህ ሥፍራ ብቻ ይገኛሉ፤ ከአምስቱ መካከል በተለይም የአንዷ ዝርያ ዓለም አቀፍ የዘርፉ ተመራማሪዎችንና ጎብኚዎች ቀልብ መሳቡ ይጠቀሳል። ከአካባቢው ተፈጥሯዊ አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ጋር መጣጣም የቻሉ የቆላ እፅዋት (ዛፎች) በምቾት በስፋት እንደሚገኙበትም ይገለጻል። የተመሠረተው በ1958 ዓ.ም ሲሆን፤ ስፉቱም 591 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ነው፤ በቁጥርም ሆነ በሥብጥር የብዙዎች መኖሪያ የሆነው ይህ ሥፍራ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ይሰኛል። መንግሥት በሰጠው ትኩረት ከነበረው በተሻለ ሁኔታ እንስሣቱም ሆኑ እፅዋቱ እየኖሩ ነው፤ ከሕገ ወጥ ድርጊትም እንዲጠበቁ ማድረግ መቻሉን የፓርኩ ኃላፊ አደም መሐመድ ለኢዜአ አረጋግጠዋል። በፓርኩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁንም ለ247 ወገኖች ቋሚ እና ለ2 ሺህ 535 ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ባሳለፍነው ዓመትም በ1 ሺህ 751 የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች እንደተጎበኘ ኃላፊው ገልጸዋል።
                         
 
                       
                          የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
                         
 
                        
                         Oct 15, 2025 728
                        
 
                         
                          አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል።   ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው።   የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።   እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።   “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው።   ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል።   ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።   የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
                         
 
                       
                           ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
                         
 
                        
                         Oct 9, 2025 702
                        
 
                         
                          ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም።   በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል።   የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል።   በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል።   ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል።   በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።   በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
                         
 
                       
                          የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
                         
 
                        
                         Oct 3, 2025 915
                        
 
                         
                          አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።  
                         
 
                       
                  ትንታኔዎች
                 
                
                          ማድያት እና ህክምናው
                         
 
                        
                         Sep 29, 2025 1543
                        
 
                         
                          ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
                         
 
                       
                          በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
                         
 
                        
                         Sep 5, 2025 2019
                        
 
                         
                          ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
                         
 
                       
                          የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
                         
 
                        
                         Aug 6, 2025 2869
                        
 
                         
                          የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
                         
 
                       
                          ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
                         
 
                        
                         Jul 19, 2025 2984
                        
 
                         
                          በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
                         
 
                       
                  ልዩ ዘገባዎች
                 
                
                          በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
                         
 
                        
                         Oct 13, 2025 833
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
                         
 
                       
                          በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
                         
 
                        
                         Oct 11, 2025 599
                        
 
                         
                          አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
                         
 
                       
                          ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
                         
 
                        
                         Mar 5, 2025 6439
                        
 
                         
                          በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
                         
 
                       
                          "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
                         
 
                        
                         Dec 13, 2024 4916
                        
 
                         
                            ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
                         
 
                       
               መጣጥፍ
              
             
                       የዳሰነቾች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ''
                      
 
                     
                      Oct 30, 2025 583
                     
 
                      
                       የዳሰነች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ''ጀለባ'' (በጣፋጩ ሰለሞን ከጂንካ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ዳሰነቾች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በአብሮነት ተጎዳኝተው ይኖራሉ። የብሔረሰቡ አባላት ዋነኛ መተዳደሪያ ከብት እርባታ ሲሆን፤ ከከብት እርባታው ጐን ለጐን በዝቅተኛ ደረጃ በግብርናና በዓሳ ማስገር ስራ ይተዳደራሉ፡፡ ዳሰነቾች በሰሜን ከሐመር፣ በደቡብ ከኬኒያ፣ በምስራቅ ከቦረና በስተ ምዕራብ ደግሞ ከኛንጋቶም ማህበረሰብ ተጎራብተው ይኖራሉ። ዳሰነቾች ከኩሽቲክ የቋንቋ ነገድ የሚመዘዝ ''አፍ ዳሰነች'' የተሰኘ የመግባቢያ ቋንቋም አላቸው። ዳሰነቾች የተለየ የአለባበስ፣ የአጋጌጥ፣ የቤት አሰራር እና የባህላዊ የሙዚቃ ስልተ ምትን ጨምሮ አስደማሚ ባህሎች እና ማራኪ የመልክዓ ምድር አቀማመጥን የታደሉ ናቸው። ዳሰነቾች ከሚታወቁባቸው አስደማሚ ባህሎች ውስጥ አንዱ የሆነው አለመግባባቶችን በውይይት የሚፈቱበት የ''ጀለባ''ስርዓት ተጠቃሽ ነው። ይህ ስርዓት ግጭቱ ቂምና ቁርሾ በማይሻገርበት መልኩ በዘላቂነት የማስወገድ አቅም ያለው ሲሆን የማይናወጥ ሰላምና ወንድማዊ ትስስር እንዲጠናከርም ሚናው የጎላ ነው። ዕሴቱ የዳሰነቾች የአኗኗር ቁመና የሚለካበትና የሚመዘንበት መጻኢንም የሚተለምበትም ጭምር ነው። ስለሆነም በዳሰነቾች ዘንድ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል ነው የሚባለው። የባህሉ ተመራማሪ ሊዮን አርሎት 'ጀለባ'' የተሰኘው ባህላዊ ዳኝነት ከአካባቢው ሰላም አልፎ ለቀጠናው ወንድማማችነት መጠናከር ትልቅ ሚና ያለው የፍትህ ስርዓት መሆኑን ያነሳሉ። በ''በጀለባ'' ስርዓት ባህላዊ የዳኝነት አሰጣጥ እርከኖች እንዳሉ ጠቅሰው፥ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ ''ኖሞ'' የተሰኙ ሽማግሌዎች ወደ ስፍራው በማቅናት የግጭቱን መንስኤ በማጣራት ''ቶሎል'' ለተሰኙ ሌሎች ሽማግሌዎች የሚያሳውቁበት አሰራርም አላቸው። እንደ ግጭቱ ቅለትና ክብደት ''ቶሎል'' በተሰኙ ሽማግሌዎች ተለይቶ ቀለል ያለው ''ካባና'' በተሰኙ ዳኞች ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን፥ ጉዳዩ ከበድ ያለ ከሆነ ደግሞ የመጨረሻው ውሳኔ ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች ይሰጣል። ከነፍስ ማጥፋት በስተቀር ሁሉም ውሳኔዎች ''አራ'' በተሰኙ ዳኞች እልባት ያገኛሉ። የነፍስ ማጥፋት ወንጀል ሲከሰት ግን ጉዳዩን ለመንግሥት አሳልፎ በመስጠት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያገኝ ይደረጋል ። ነፍስ ያጠፋው ሰው የእርምት ጊዜውን አጠናቆ ማህበረሰቡን ለመቀላቀል ሲወስን ባህላዊ የዕርቅ ስነ-ስርዓት ተዘጋጅቶ በዳይና ተበዳይ ይቅር የሚባባሉበትም ስርዓት እንዳለ የባህሉ ተመራማሪ ይናገራሉ።   በዳሰነቾች ባህል ልዩነቶች ሰላማዊ በሆነ መንገድ በዘላቂነት መንገድ የመፍታት ዘመናትን የተሻገረ ድንቅ ዕሴት መኖሩን የሚያነሱት የብሔረሰቡ አባል አሸቴ ነካሲያ፤ “በዳሰነች ብሔረሰብ ቂም መያዝ አሎሎ ተሸክሞ እንደመዞር ይቆጠራል'' ይላሉ። በዳሰነቾች አለመግባባቶች በውይይት የሚፈቱበት ስርዓት እንዳለ ጠቅሰው፥ ''ናብ'' በተሰኘው የዳኝነት ስፍራ አለመግባባቶች ውለው ሳያድሩ እልባት ያገኛሉ ብለዋል። ሌላው የብሔረሰቡ አባል ሎቶያቡስ ሎኪሰሬሬ በበኩላቸው የባህል መሪዎች የተጣላን ማስታረቅ፣ ትውልዱን የመግራትና በስነ-ምግባር የማነፅ ኃላፊነት እንዳላቸው ጠቅሰዋል። ''ማንም ሰው ከባህል መሪዎች ትዕዛዝ አያፈነግጥም'' የሚሉት አቶ ሎቶያቡስ፥ ሁሉም እርስ በእርስ በመከባበር እና ችግሮች ሲኖሩ በውይይት በመፍታት አብሮነቱን ያጠናክራል ብለዋል።   ወጣቱ ለባህል መሪዎች ታዛዥ ነው የሚሉት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ የብሔረሰቡ አባል ሎሲያ ሎብቻ ወጣቶች ለአካባቢው ሰላም ዘብ እንዲቆሙ፣ ከአጎራባች ህዝቦች ጋር በፍቅር እንዲኖሩ በማስተማር ወጣቱን በስነ-ምግባር የማነፅ ስራ እንደሚሰሩም ተናግረዋል። የዳሰነች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ በበኩላቸው የዳሰነች ህዝብ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴ ከወረዳው አልፎ ለቀጠናው ሰላም ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። የብሔረሰቡ ባህላዊ የሽምግልና ስርዓት ትውልዱን በመግራት በስነ- ምግባር የታነፀ ዜጋ እንዲፈጠር እንዳደረገም አስረድተዋል።   የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የሶሻል አንትሮፖሎጂ መምህርና ተመራማሪ አጎናፍር ሰለሞን፤ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓቶች ለዘመናዊው የፍትህ ስርዓት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል ብለዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች ቅጣት በመጣል ጥፋተኝነት እንዲሰማ የሚያደርጉ ሳይሆኑ፤ እውነተኛ ይቅርታን የሚያሰፍኑና ለአብሮነት የሚበጁ ዕንቁ ባህሎች እንደሆኑም አብራርተዋል።   ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹ በግለሰብ ተጠቃሚነት ላይ ሳይሆን በማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት የሚያደርጉ በመሆናቸው ከዘመናዊው የፍትህ ስርዓት በይበልጥ ለአብሮነት መጠናከር አስተዋጽኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል። ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎቹም ለሀገራዊ መግባባት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ፥ እሴቶቹ ተጠብቀው፣ ለምተውና ጎልብተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት እንደሚገባም መክረዋል። ሀገራችን ቂምና ቁርሾን የወለዱ ያለመግባባቶች በዘላቂነት በሰለጠነና ሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ሁሉንም ያሳተፈ ስራ እየሰራች እንደሆነ ያነሱት መምህርና ተመራማሪው አጎናፍር ሰለሞን ዕሴቶቹ በማህበረሰቡ ዘንድ ካላቸው ተቀባይነት እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ሂደቱን ከማገዝ አንጻር ጉልህ ሚና ስለሚኖራቸው መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
                      
 
                    
                       ''ቦር ተራራ'' የየሞች የፈውስ ምድር 
                      
 
                     
                      Oct 27, 2025 324
                     
 
                      
                       (በእንዳልካቸው ደሳለኝ ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) የም ዞን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ይገኛል። በዞኑ የቦር ተራራ ዋነኛው የመድኃኒት እጽዋት መገኛ እና ምንጭ በመሆኑ የሞች በየዓመቱ ጥቅምት ወርን ጠብቀው በ17ኛው ቀን ከዚህ ተራራ በህብር ሆነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስነ-ስርዓት ያካሂዳሉ፤ ይሰባስባሉም ። የቀደምት የየም አባቶችና እናቶችን በማሳተፍ የሚከወነው የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ከባህር ጠለል በላይ 2 ሺህ 939 ሜትር ከፍታ ላይ በሚገኘው ቦር ተራራ ላይ ነው። በዚህ ተራራ ላይ በየዓመቱ ጥቅምት 17 ቀን የሞች ለዓመት የሚያገለግላቸውን የመድኃኒት እጽዋት ይለቅማሉ። ተግባሩንም አዋቂዎች በጋራ ሰብሰብ ብለው ለመድኃኒት የሚውለውን ቅጠል በጥሰው፣ ስር ምሰው፣ አስሰውና መርጠው ይሰበስባሉ። ይህም የመድኃኒት እጽዋት ለቀማ ስርዓት "ሳሞ ኤታ" ተብሎ ይጠራል ። አያምጣውና ህመም ሲከሰት ታማሚውን ሰው ወይም እንስሳን ከበሽታው ለመፈወስ የተዘጋጀው ባህላዊ መድሃኒት በባህላዊ ሃኪም ትዕዛዝ መሰረት በህመሙ ልክ ይታዘዝለታል። መድሃኒቱን ለመጠቀምም የጠቢባን አባቶችን ፈለግ ተከትሎ መፈፀም የግድ ይላል። የሞች አጅግ አስገራሚ እና አስደናቂ የሆኑ የበርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤት ናቸው ካስባሏቸው እሴቶች መካከል ይህ ለየት ያለው ክዋኔያቸው አንዱ ነው፡፡ አባቶች ታዳጊና ወጣቶችን አስከትለው ወደ ቦር ተራራ በመውጣት የሚፈፅሙት ባህላዊ ክዋኔ በመሆኑም ከትውልድ ወደ ትውልድ ቅብብሎሹን ጠብቆ እስከ አሁን እንዲዘልቅ እድርገውታል።   በየሞች ዘንድ የባህላዊ መድኃኒት አዋቂዎች ከሚባሉት መካከል አንዱ አቶ ጌታቸው ሃይለማርያም፤ የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ልምድን የቀሰሙት ከአባታቸው መሆኑን በመግለፅ አያታቸው ከቅድመ አያቶቻቸው በመውረስ እዚህ እንዳደረሱት ይናገራሉ። የቦር ተራራ ለመድሃኒት ዕፅዋት ለቀማው የተመረጠበትን ምክንያት ሲያስረዱም ቦታው ተራራ በመሆኑ ማንም ያልደረሰባቸው የተለያዩ እፅዋትን ለማግኘት አመቺ ከመሆኑ ጋር ያያይዙታል። በሌላም በኩል ጠዋት ፀሐይ ስትወጣ መጀመሪያ የምታገኘው ተራራውን በመሆኑና ክረምቱ አልፎ ጥቅምት ሲገባ የተለያዩ ቅጠላ ቅጠሎችን በብዛት እና በዓይነት ለማግኘት ተመራጭ ወቅት መሆኑም ቦታው የተመረጠበት ሌላኛው ምክንያት ነው ብለዋል። በጥቅምት 17 ለመድኃኒትነት የሚያገለግለው ዕፅዋት ቅጠልም በየፈርጁ ተለቅሞ እና ተቀምሞ ይቀመጣል ሲሉም አስረድተዋል። የተዘጋጀው ባህላዊ መድኃኒትም ለሰው ልጆችና ለቤት እንስሳት ያገለግላል ሲሉም አስረድተዋል፡፡ ይኸው በዚህ ቀን የተለቀመው የመድኃኒት ዕፅዋት ከዚህኛው ጥቅምት 17 እስከሚቀጥለው ዓመት ጥቅምት 17 ድረስ እንደሚያገለግልም አቶ ጌታቸው አስረድተዋል፡፡ የባህል መድኃኒት ሰብሳቢዎች እና ተጠቃሚዎች ጊዜውን ጠብቀው ከተለያዩ ቦታዎች ወደ ቦር ተራራ እንደሚመጡ የሚገልጹት የባህል መድኃኒት አዋቂው ዛሬ ዛሬ እሳቸውን ጨምሮ መድኃኒት ቤቶችን በመክፈት ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ የባህል መድኃኒቶችን በመሸጥ ኑሯቸውን እየመሩ የሚገኙ አያሌ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉም ይናገራሉ። ሌላኛው የባህል መድኃኒት አዋቂው አቶ ወልደመስቀል ጆርጋ በበኩላቸው በየሞች ዘንድ የተዘጋጀው የመድኃኒት ዕፅዋት ጥቅም ላይ የሚውለው ህመም ሲያጋጥም ብቻ ሳይሆን በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል መሆኑን ጠቁመው መድኃኒቶቹም ብቻቸውን እንዲሁም ከምግብ ጋር በመመገብ ለጥቅም እንደሚውሉም አንስተዋል። የየም ምድር የበርካታ የመድኃኒት ዕፅዋቶች መገኛ አካባቢ " የፈውስ ምድር " ነው የሚሉት ደግሞ በየም ባህላዊ መድኃኒት ዙሪያ ጥናት ያደረጉት በጅማ ዩኒቨርሲቲ የፎክሎር መምህር እና ተመራማሪ ለማ ንጋቱ (ዶ/ር) ናቸው። ከየሞች አያሌ የባህል ዕሴቶች መካከል የባህል መድኃኒት ለቀማና ቅመማ አንዱና ዋነኛው የሀገር በቀል እውቀት ማሳያ መሆኑን ገልፀው የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማ ስነ-ስርዓቱ ከጥንት ጀምሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ዛሬ ላይ የደረሰ እንደሆነም ያስረዳሉ፡፡   ማህበረሰቡ የራሱንም ሆነ የእንስሳትን ጤና የመጠበቅ የቆየ ባህል ያለው መሆኑን በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው የባህላዊ መድኃኒት ለቀማው ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚሳተፉበት ዓመታዊ ክዋኔ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ሌላው ገራሚው ነገር ይላሉ አጥኚው ታላላቆች ታናናሾቻቸውን አስከትለው የለቀማ ሂደቱን የሚያስረዱበት መንገድ ደግሞ ስርዓቱ ለመጪው ትውልድ እንዲተላለፍ የሚያስችል ትውልድ ተሻጋሪ የሀገር በቀል እውቀት ሽግግር ስርዓት ማሳያ እንደሆነም ነው የገለጹት። በዚህም ሂደት የሚነገሩ ስነ-ቃሎች መሞጋገስ፣ ጭፈራና ደስታ ይስተናገድባቸዋል። ይህም ማህበራዊ ትስስርን ይበልጥ የሚጠናክሩበትን ሁነት የሚፈጥር ስርዓት ነው። የየም ዞን ባህል እና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ሞጋ በበኩላቸው የቦር ተራራ የመጀመሪያውን የማለዳ የፀሐይ ጎህ የሚፈነጥቅበት የንጋት ብርሃን ቀድሞ የሚያገኝ በመሆኑ፥ በዚህ አካባቢ የሚገኙ እጽዋት በሽታን የመከላከልና ፈዋሽነታቸው ከፍተኛ ነው ተብሎ ስለሚታመን ለዚህ ክዋኔ ቦታው መመረጡን ነው የሚገልፁት። ለዚህም ነው የሞች ይህንን ስፍራ ከሌሎች ቦታዎች አስበልጠው የሚወዱት፤ በየዓመቱም ጥቅምት 17 ቀን ወደ እዚህ ስፍራ በማቅናት ለዓመት ፍጆታ የሚያገለግላቸውን መድኃኒትም ይሰበስቡበታል ብለዋል። ጥቅምት 17 በየም ዘንድ ለየት የሚያደርገው ሌላው የመድሃኒት ዕፅዋት ለመልቀም እና ለመጠቀም ብቻ ሳይሆን የለቀማውን ትዕይንት ለመመልከት የሚመጡ ቱሪስቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸው ሌላው ትልቁ ትሩፋት ነው ይላሉ። የመድኃኒት ዕፅዋት ለቀማው ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት በመሆኑ፥ ለአብሮነት እና ሃገር በቀል እውቀት ለመቅሰም ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ነው አቶ መስፍን የገለፁት።    
                      
 
                    .jpg) 
                        
                        
                       .jpg) 
                       .jpg) 
                       .jpg) 
                       .png) 
                       .png) 
                        
                       .png) 
                        
                          .jpg) 
                          .png) 
                          .png) 
                           
                           
                           
                          .jpg) 
                           
                              
                              
                              
                             .jpg) 
                             .jpg) 
                        
                       .jpg) 
                        
                        
                          .jpg) 
                           
                           
                          .jpg) 
                           
                           
                           
                           
                          .jpg) 
                           
                           
                           
                           
                           
                           
                          .png) 
                           
                          .jpg) 
                           
                           
                           
                          .png) 
                           
                           
                           
                           
                        
                        
                        
                        
                       .jpg) 
                        
                        
                       