ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 24, 2026 0
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት በከተማዋ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታን በለሚ ኩራ ከፍለ ከተማ ተገኝተው በይፋ አስጀምረዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፥ የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታው ወጣቶችን በክህሎት በማልማት የሀገርን እድገት ለማፋጠን ያለመ ነው ብለዋል። ባለፉት የለውጥ አመታት በመዲናዋ ወጣቶች የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ላይ ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል። እነዚህ በክህሎትና በቴክኖሎጂ የበቁ ወጣቶች አሁን ላይ ከራሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው አልፈው በሀገር ሁለንተናዊ እድገት ላይ የበኩላቸውን አሻራ እያሳረፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል። አሁን ላይ ወጣቶችን ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ልክ የማብቃት ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። አዲሱ ስማርት ፖሊቴክኒክ የጀርመንን የቴክኒክና ሙያ ልምድ መነሻ በማድረግ፣ በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚገነባና ትውልድ ተሻጋሪ እውቀት የሚገበይበት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኮሌጁ ወጣቶች እውቀትን የሚታጠቁበት፣አዕምሮ እና የሚሰሩ እጆች ተጣጥመው ሀሳብ የሚያፈልቁበት መሆኑን ገልጸዋል። ኮሌጁ በአመት በርካታ አዳዲስ ሰልጣኞችን የመቀበል አቅም እንደሚኖረው ጠቁመው፤ በዘመናዊ ማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሙኒኬሽንና በቴክስታይል ቴክኖሎጂ መስኮች ያሰለጥናል ብለዋል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ፣ በጀትና ጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከተማ አስተዳደሩ በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ በበኩላቸው፤ የሚገነባው ኮሌጅ ወጣቶች በስልጠና ወቅት የሚያመጧቸውን የቴክኖሎጂ ሀሳቦችና የምርምር ውጤቶች ወደ ተግባራዊ ቢዝነስ እንዲቀይሩ፣የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ እንዲመሰርቱና ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ ቅርሶችን በመጠበቅ ለሀብት ምንጭነት ለማዋል እየተሰራ ነው
Jul 24, 2026 10
ጎንደር፤ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ጥንታዊ ቅርሶችን በመጠገን፣ በማደስና በዘመናዊ ሥርዓት በመያዝ የሃብት ምንጭ ሆነው እንዲቀጥሉ እየተሰራ ያለው ስራ ውጤታማ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ገለጹ። የባለስልጣኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በጎንደር ከተማ የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ነባር ቅርሶችን በማደስና አዳዲስ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የሀብት ምንጭ የማድረግ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቷቸዋል። በዚህም ቅርሶችን በመጠበቅ፣ በመንከባከብና በማደስ የኢኮኖሚ ምንጭ የማድረግ ፍልስፍናው በተሳካ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የጎንደር አብያተ መንግስታትን፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የጅማ አባጅፋር ቤተ መንግስትን፣ የሐረር ቅርሶችንና የነቀምት የቁምሳ ሞረዳ ቤተመንግስት እድሳት ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም በዋና ዋና የቅርስ መገኛ አካባቢዎች ሙዚየሞችን በማስገንባት እና ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን ለጎብኝዎች ክፍት በማድረግ የሀብት ምንጭ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። የአዝማሪ ጨዋታዎችን ጨምሮ የሀገር ባህል ዘፈኖችና ጭፈራዎችን ወደ አደባባይ በማውጣት የገጠሩን ቱሪዝ ልማት በማሳደግ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የጎንደር ከተማ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ማርያም ካሳሁን እንደገለጹት፣ በከተማዋ የተከናወነው የኮሪደር ልማትና የታሪካዊ አብያተ መንግስታት እድሳት የቱሪዝሙ ዘርፉን እንዲነቃቃ አድርጓል። በዚህም በ2017 በጀት ዓመት አንድ ሺህ 914 የነበረው የውጭ ሀገር ቱሪስቶች ቁጥር በ2018 በጀት ዓመት ወደ ስድስት ሺህ 420 ማደግ መቻሉን በማሳያነት አቅርበዋል። ባለስልጣኑም በጎንደር ከተማ ለሚገኘው የደብረ ብርሃን ሥላሴ ጥገና በመጀመሪያው ምእራፍ 30 ሚሊዮን ብር መመደቡን ጠቁመው ሌሎች ቅርሶችንም ደረጃ በደረጃ እንደሚታደሱ ነው የተናገሩት። ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹ በቅርቡ የታደሰው የፋሲል አብያተ መንግስትን ጨምሮ ሌሎች በከተማዋ የሚገኙ የመስህብ ህብቶችን ጎብኝተዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ አስጀመሩ
Jul 24, 2026 9
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት ከሰዎች ለሰዎች ድርጅት ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ አስጀምረዋል። የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታው ሲጠናቀቅ ወጣቶችን በማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሪክና ኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሙዩኒኬሽንስ፣ በቴክስታይል እና የሲኤንሲ (CNC) ቴክኖሎጂዎች ላይ ተግባር ላይ ያተኮረ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም ሥልጠና እንደሚሰጥ ከንቲባዋ ገልጸዋል። ሀገርን ማልማት እና ከድህነት መላቀቅ በንድፈ ሐሳብ ብቻ በተገደቡ ትምህርቶች ማሳካት ስለማይቻል፣ ሐሳብን የሚያፈልቁ አዕምሮዎችን እና የሚሠሩ እጆችን ያጣመረ ክህሎት መር የሰው ኃይል እጅግ አስፈላጊ መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አመልክተዋል። ዛሬ ያስጀመርነው ፕሮጀክት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ወጣቶቻችንን ከሥራ ፈላጊነት ወደ ሥራ ፈጣሪነት፣ ከንድፈ ሐሳብ ወደ ተግባር የሚያሸጋግር፣ አዲስ የሥራ እድል የሚፈጥር የክህሎት ድልድይ የሚሆን ነው ብለዋል። የዚህ ኮሌጅ ግንባታ በጥራትና በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በልዩ ትኩረት የምንከታተለው ይሆናልም ነው ያሉት። ፕሮጀክቱን በትብብር የሚገነባው የረጅም ጊዜ የልማት አጋር የሆነው ሰዎች ለሰዎች ድርጅት እና የሚሠራው ለትውልድ የሚሻገር ዐሻራ ነው በማለት መሬታቸውን ለፕሮጀክቱ የለቀቁ አርሶ አደሮችንም አመስግነዋል።
የበጎ ፈቃድ ነጻ የሕክምና አገልግሎት የጤና አገልግሎትን ለሁሉም ማህበረሰብ ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ ጤናማ ዜጋ ለመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው
Jul 24, 2026 104
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የበጎ ፈቃድ ነጻ የሕክምና አገልግሎት የጤና አገልግሎትን ለሁሉም ማህበረሰብ ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ ብቁና ጤናማ ዜጋ ለመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ፡፡ «በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ» በሚል መሪ ሐሳብ የጤና ሚኒስቴር ከቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በጋራ ያዘጋጀው የክረምት የበጎ ፈቃድ የነፃ የጤና ምርመራ፣ ምክርና ሕክምና አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በጉለሌ ክፍለ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወነው የክረምት የበጎ ፈቃድ ሕክምና አገልግሎት ዋና ዓላማ በሽታዎችን ቀድሞ መከላከልና መለየት ላይ ያተኮረ ነው። ይህ አገልግሎት ዜጎች ቀድመው ሕክምና የሚያገኙበት ትልቅ ዕድል መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ዶክተር አብረሃም እሸቴ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በየዓመቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንደሚያካሂድ ጠቁመዋል። በዘንድሮው የክረምት መርሃ ግብርም ከ120ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተለያዩ ነፃ የሕክምና አገልግሎቶችን ለማቅረብ መታቀዱን ገልጸዋል። አገልግሎቱም ከተለመዱት መደበኛ ምርመራዎች ባሻገር የቀዶ ሕክምና፣ የስፔሻሊቲ ሕክምናዎች እንዲሁም እንደ ሲቲ ስካን (CT Scan) እና ኤም አር አይ (MRI) ያሉ የላቁ የዲያግኖስቲክ ምርመራዎችን ያካተተ መሆኑን አስረድተዋል። የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ከሕክምና ሥራዎች ጎን ለጎን በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን መተከል፣ የአቅመ ደካሞች ቤቶችን ማደስ፣ ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግና የማዕድ ማጋራትን እንደሚያካተት ተጠቅሷል፡፡
የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
Jul 24, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የጀርመን እግር ኳስ ፌዴሬሽን የርገን ክሎፕን የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የ59 ዓመቱ ጀርመናዊ የአራት ዓመት ውል የተፈራረሙ ሲሆን ስምምነቱ አሰልጣኙን እስከ 2030 የዓለም ዋንጫ መጨረሻ ድረስ የሚያቆያቸው ነው። ክሎፕ በቦታው የተኩት በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ጀርመን በ32ቱ ዙር በፓራጓይ ተሸንፋ ከውድድሩ ውጪ ከሆነች በኋላ ከኃላፊነታቸው የለቀቁትን ጁሊያን ናጌልስማንን በመተካት ነው። ከሊቨርፑል የዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ የሬድ ቡል ሳልስበርግ የዓለም እግር ኳስ ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት ክሎፕ፣ የጀርመን እግር ኳስን እንደገና ወደ ቀደመ ገናናነቱ የመመለስ ትልቅ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ክሎፕ ከጀርመን ብሔራዊ ቡድን ጋር የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም. በዩኤፋ ኔሽንስ ሊግ (Uefa Nations League) ከኔዘርላንድስ ጋር ያደርጋሉ።
ፖለቲካ
ሀገራዊ ምክክር የጋራ አሸናፊነት ማብሰሪያ፤ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ማሳለጫ ነው-የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች
Jul 23, 2026 316
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክር የጋራ አሸናፊነት ማብሰሪያ፤ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ማሳለጫ መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን በማወያየት ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምክክር ማድረግ ጀምረዋል። በዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪ አቶ አህመድ ሁሴን ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምክክሩ አንዱ የሌላውን ፍላጎት እና አተያይ በአግባቡ እንዲረዳ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነው። ከዚህ ቀደም ሩቅ ሆኖ በአጀንዳዎች ላይ የግል ምልከታን ማንጸባረቅ የተለመደ ነበር ያሉት አመካካሪው፤ አሁን ግን የሌሎችን ስጋት እና ፍላጎት በደንብ ለማየት ልዩ የሆነ እድል መፈጠሩን አንስተዋል። ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ ባህል እና ልምምድ መሆኑን የገለጹት አቶ አህመድ፤ በምክክር ጉባኤው ለሀገር ግንባታ ገንቢና ጠቃሚ ሀሳቦች እየተነሱበት መሆኑን ጠቁመዋል። የምክክር ጉባኤው አሳታፊ እና አካታች መሆኑ የዜጎችን መተማመን እንደሚያሳድገው ጠቅሰው፤ ይህም ለሀገር መንግሥት ግንባታ እንዲሁም ለሀገር ግንባታ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። ከተመካካሪዎቹ መካከል አቶ መልካሙ ጸጋዬ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም በተቃርኖ ጫፍና ጫፍ ሆነን ስንወጋገዝ ኖረናል ብለዋል።ምክክሩ ለኢትዮጵያ ሁሉም የድርሻውን የሚያበረክትበት አውድ የፈጠረ መሆኑንም ተናግረዋል። በምክክሩ ልማትን ለማፋጠን የሚረዱና የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ሀሳቦች እንደሚፈልቁበት ያላቸውን እምነት ገልጸው፤ ለዚህም እንደ አንድ ተመካካሪ የድርሻዬን ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብለዋል። ምክክር የሁሉ ነገር መፍቻ ቁልፍ በመሆኑ ልዩነትን በኃይል ሳይሆን በምክክር የመፍታት ግብ ይዘን ወደ ምክክሩ መጥተናል ያሉት አቶ መልካሙ፤ የጋራ አሸናፊ የሚያደርገን ይሄው መንገድ ብቻ መሆኑን ገልጸዋለ። ሌላው ተመካካሪ ወጣት ዮሴፍ አበራ በበኩሉ፤ በምክክሩ ላይ በመሳተፌ ብዙ ልምድ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርጉ ሀሳቦች እየመነጩበት መሆኑን መታዘቡን ገልጿል። ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር ወሳኝ እርምጃ ላይ ነን ያለው ወጣት ዮሴፍ፤ ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርግ ሀሳብ ይዘን ተነስተናል እንደሚሳካም ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ ብሏል።
የሃሳብ መቀራረብን በማጠናከር የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ የሚገነባ ምክክር እያደረግን ነው - የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች
Jul 23, 2026 290
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦ በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ያለምንም ገደብ የሃሳብ መቀራረብንና የጋራ መግባባትን በማጎልበት የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ የሚገነባ ምክክር እያደረጉ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በንዑስ ቡድኖች ተከፋፍለው በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተመካከሩ ነው። የምክክር ጉባኤው ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፣ በኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆዩ ያለመግባባት ጉዳዮችን ለመፍታት በተሰባሰቡ የሕዝብ ወኪሎች እየተካሔደ ያለው ምክክር ለቀጣዩ ትውልድ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ነው። በምክክር ጉባኤው ላይ የሚመከርባቸው አጀንዳዎችም የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ በማጎልበት ሀገራዊ አንድነትን፣ መከባበርንና ዘላቂ መግባባትን የሚያጠናክሩ እንደሆኑም ገልጸዋል። ተመካካሪ ሊቀ ካህናት መልዓከ ሰላም ጌታሰው በላይ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው የሁሉም ዜጎች የሕዝብ ወኪሎች በአንድ መድረክ ተሰባስበው እየመከሩበት የሚገኝ ታሪካዊ ዕድል ነው። ስለ ሀገር አንድነት፣ ሰላምና መግባባት እየመከርን ነው ያሉት ሊቀ ካህናት መልዓከ ሰላም ጌታሰው በላይ፣ በቀጣይም ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት እንዲገነባ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ሌላኛው ተመካካሪ ፓስተር ጻዲቁ አብዶ በበኩላቸው፣ ምክክር በኃይማኖታዊ አስተምህሮ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው እሴት መሆኑን ጠቅሰዋል። ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤም ለአሁኑና ለመጪው ትውልድ ጠቃሚ ትምህርት የሚያስተላልፍ የኢትጵያዊያን የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ የሐሳብ መሸናነፍ ሳይሆን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የጋራ አሸናፊ ለማድረግ የሚያስችል የመግባባት ሂደት መሆኑንም አመልክተዋል። ተመካካሪ አባገዳ ደቻሳ ወዳጆ በበኩላቸው፣ ምክክሩ ለትውልድ ተስፋ የሚጣልበት ታሪካዊ የተሞክሮ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ሕዝቡም በተስፋ የሚጠብቀው ሂደት በመሆኑ ስለ ኢትዮጵያ ቀጣይ ዕድገትና ልማት በማሰብ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ በበኩላቸው፣ በምክክሩ የሕዝብ አጀንዳዎችን በነፃነትና በተገቢው መንገድ የሚያቀርቡበት ምቹ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በዚህም በተመረጡት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ጥልቅና ገንቢ ምክክር እያካሄዱ መሆኑን ገልጸዋል። ለሀገራችን ይጠቅማሉ ብለን በምናምንባቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ወደ መግባባት ለመድረስ እየሠራን ነው ብለዋል። ተመካካሪ አቶ ሳይመን ቶት በበኩላቸው፣ ምክክሩ የመወያየትና የመደማመጥ ባህልን ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፍ ጠንካራ መሠረት በመጣል መግባባት የሰፈነባትን ሀገር ለመገንባት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነት መሰረት የሚጥል ነው
Jul 23, 2026 305
ደሴ ፤ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነት መሰረት የሚጥል መሆኑን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የሐይማኖት አባቶች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ባሰባሰባቸውና በተለዩ ስምንት አጀንዳዎች ላይ የዋናው የምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የኢትዮጵያን የቆዩ ችግሮች በምክክር በመፍታትና ለሁሉም የምትመች ጠንካራ ሀገር የመገንባት ትልም ተይዞ እየተሰራ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የባቲ ከተማ የሃይማኖት አባት መላከ ፀሐይ ሰምረ አስቻለው እንዳሉት፥ ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነትን ለማምጣት መሰረት የሚጥል ነው ። በምክክሩ የመደማመጥ እሴትን በመጠቀምና በማጎልበት ለችግሮች መፍትሄ ማስቀመጥ ይገባል ብለዋል። ለምክክሩ በአጀንዳነት የተመረጡ ጉዳዮችም ችግሮቹን ለመፍታት መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ጠቁመው፥ለጉባኤው ስኬት ሁሉም ሀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ መክረዋል። ሌላው የሰንበቴ ከተማ የሐይማኖት አባት ሸህ ኡመር ሸህ መሀመድ በበኩላቸው፣ የምክክር ኮሚሽኑ እየሄደበት ያለው እርቀት በኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ስኬት ነው ብለዋል። በምክክሩ የሚነሱ ችግሮች መፍትሔ የሚያገኙበት ከመሆኑ ባለፈ ለመጪው ትውልድ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለማስተላለፍ የሚያግዝ እንደሚሆን ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው በተለዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ መፍትሄ በማምጣት የሕዝቦችን አብሮነት ያጠናክራል ብለው ተስፋ ማድረጋቸውን የሀይማኖት አባቶቹ አመላክተዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ነው-ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jul 23, 2026 396
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሂደት በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ዋናውን የምክክር ጉባኤ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፣ ምክክሩ አጀንዳዎችን በማብላላትና በምሁራን ገለጻዎች ተደግፎ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል። ባለፉት ቀናት በተከናወኑ የምክክር መድረኮች ተመካካሪዎች በቡድን ተከፋፍለው የተሰጧቸውን አጀንዳዎች በጥልቀት በማብላላት፣በመደማመጥና በመከባበር ወደ ሐሳብ ማጠናቀር ሂደት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው የምክክር ጉባኤም ተመካካሪዎች በ50 እና በ10 አባላት በመከፋፈል የመጀመሪያውን የሐሳብ ማመንጨትና ማጠናከር ሂደት ማከናወናቸውን ተናግረዋል። በ10 አባላት በመደራጀት የተካሄደው ውይይት በተመካካሪዎች መካከል የልብ ቅርርብ በመፍጠር እንዲተዋወቁና በተሰጧቸው አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት እንዲመክሩ ማስቻሉን አስረድተዋል። በዚህም ሂደት ተመካካሪዎች እርስ በእርሳቸው እንዲቀራረቡና አጀንዳዎችን በጥራት እንዲያብላሉ በተዘረጋው አሠራር መሠረት ውጤታማ ሥራ መሠራቱን አመልክተዋል። 10 አባላት ባሏቸው ቡድኖች በተካሄደው ምክክር የተጠናቀሩ ሪፖርቶች ላይ ከነገ ጀምሮ 50 አባላት ባሏቸው ቡድኖች በመሰባሰብ ውይይት እንደሚጀመር አስታውቀዋል። በዛሬው ዕለትም ሙያተኞች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በስምንት ቡድኖች ለተከፋፈሉ ተመካካሪዎች ሰፊ ማብራሪያዎችንና መረጃዎችን መስጠታቸውን ገልጸዋል። በሀገር ግንባታ፣ በታሪክ፣ በፌዴራሊዝምና በማንነት ጉዳዮች ላይ በቂ እውቀትና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች ለተመካካሪዎች ልዩ ግብዓት የሚሆን ገለጻ በማቅረብ፣ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ መስጠታቸውን አስረድተዋል። ከነገ ጀምሮም 10 አባላት ባሏቸው ቡድኖች በተካሄደው ምክክር ያጠናቀሯቸውን ሪፖርቶች ለ50 አባላት ባሏቸው ቡድኖች በማቅረብ የቀጣዩ የውይይት ሂደት እንደሚጀመር ገልጸዋል። በምክክር ጉባኤው 4 ሺህ ተመካካሪዎችን ማስተናገድ ሰፊ ዝግጅት የሚጠይቅ ቢሆንም፣ የጤና፣ የጸጥታና ደህንነት፣ እንዲሁም የትራንስፖርት ተቋማት እያደረጉት ያለውን የተቀናጀ ድጋፍ አድንቀዋል። የተከናወኑት የውይይት ሂደቶች በስምንቱም ቡድኖች ውስጥ በ500 ተሳታፊዎች ተደራጅተው ሲካሄዱ ቆይቷል ብለዋል። ከነገ ጀምሮ 50 አባላት ያሏቸው ቡድኖች ያጠናከሯቸውን ሪፖርቶች ለቡድኖቻቸው በማቅረብ ወደ 250 አባላት ባሏቸው ሃምሳ ቡድኖች የሚደረገው ቀጣይ የውይይት ሂደት እንደሚሸጋገር ገልጸዋል። በቀጣይ ሳምንት ደግሞ 4 ሺህ ተሳታፊዎች በ16 ቦታዎች ተከፋፍለው የምክክር ሂደቱን እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል። በውይይቱ ወቅት ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ተሳታፊዎች በፌዴራልና በክልል ሆስፒታሎች ተገቢውን የሕክምና አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም የጸጥታና ደህንነት፣ የትራንስፖርትና ሌሎች ድጋፍ ሰጪ ተቋማት ለተሳታፊዎች አስፈላጊውን አገልግሎት በተቀናጀ መልኩ እየሰጡ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ስር የሰደዱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል ምክክር እያደረግን ነው
Jul 23, 2026 344
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ምክክሩ ስር የሰደዱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የተሻለች አገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችል ምክክር እያደረግን ነው ሲሉ በምክክሩ በመሳተፍ ላይ የሚገኙ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ማህበረሰብ አባላት ገለፁ። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት አጀንዳዎች ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም 4 ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምክክር ማድረግ ጀምረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጰያዊያን እንዳሉትም፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ግልጽና ተስፋ ሰጪ በሆነ መንገድ እየተካሄደ ነው። ምክክሩ የመደማመጥና የጋራ መግባባት ባህልን በማጠናከር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ዕድል መሆኑንም ጠቅሰዋል። ከተመካካሪዎች መካከል አገርነሽ ሃይሌ በሰጡት አስተያየት፤ የምክክር ሂደቱ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ፣ አካል ጉዳተኞችን፣ ሴቶችን፣ ወጣቶችን እና ሌሎችንም የህብረተሰብ ክፍሎች ማካተቱ እጅግ አሳታፊ እንዲሆን አድርጎታል ብለዋል። ለምክክር ሒደቱ ስኬታማነት የድርሻቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት በንቃት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም እና ልማት ቅድሚያ በመስጠት በምክክር ሂደቱ ስኬታማነት አዎንታዊ ሚናችንን መጫወት ይኖርብናል ብለዋል፡፡ ተመካካሪ ወይዘሮ ፎዚያ ሁሴን በበኩላቸው፤ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተርፉ አጀንዳዎች ላይ እየተወያየን በመሆናችን ነገን በሚያሻግር መልኩ የተሰጠንን አደራ በከፍተኛ ኃላፊነት እንወጣለን ብለዋል፡፡ ሁላችንም የተሰጠንን ይህንን ታሪካዊ አደራ በከፍተኛ ኃላፊነት በመወጣት፣ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም እና አንድነት በጋራ መቆም አለብን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ህገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልልን ሕዝብና ተተኪውን ትውልድ ለከፋ አደጋና ጉስቁልና እየዳረገ ነው
Jul 23, 2026 433
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይን ሕዝብና ተተኪውን ትውልድ ለከፋ አደጋና ጉስቁልና እያዳረገ መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የቀድሞ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። የትግራይ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ትዴፓ) ሊቀ-መንበር አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ህገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን ከተመሠረተበት ማግሥት ጀምሮ ችግሮችን በጠመንጃ አፈሙዝ ለመፍታት የሚሞክር ግትር አቋም ያለው የወንጀለኞች ስብስብ ነው። በፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በተገቢው መንገድ ተግባራዊ እንዳይሆን እንቅፋት ሲፈጥር የቆየው ህገወጥ ቡድኑ፤ በአሁኑ ወቅት ሰላማዊ የፖለቲካ አማራጮችን በመዝጋትና ከሻዕቢያ ጋር ያልተቀደሰ ጥምረት በመፍጠር የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር በመፈንቅለ መንግሥት ማፍረሱንም አክለዋል። በተጨማሪም ወጣቶችንና ሕፃናትን ከቤተሰቦቻቸው በመንጠቅ ወደ ጦር ካምፕ በማስገባት ለተለያዩ አካላት የገቢ ምንጭ እያደረጋቸው ይገኛል ብለዋል። የፌዴራል መንግስት ለህገ-ወጡ ቡድን የሚያቀርበው ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ እና የሚያሳየው ትዕግሥት የሕዝቡን ጉስቁልና ለማስቀረት ያለመ መሆኑን አንስተዋል፡፡ የትግራይ ክልል የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር እና የዓረና ሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ገብሩ አስራት በበኩላቸው፤ ህገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን ሻዕቢያን ጨምሮ ከተለያዩ ህገ-ወጥ ኃይሎች ጋር በመጣመር የትግራይን ሕዝብ ለከፋ ጉዳት የሚዳርግ የጥፋት ተግባር ላይ በመሰማራት ጠላትነቱን በተጨባጭ ማረጋገጡን ተናግረዋል። ቡድኑ ለሥልጣን ሲል ከክልሉ ሕዝብ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመተባበር ለሌላ ግጭት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ሻዕቢያ የትግራይን ሕዝብ ለማጥፋት የሚጥር መሆኑን ቀደም ሲል በክልሉ የፈጸመው ጭፍጨፋና ያስከተለው ውድመት ማረጋገጫ ነው ብለዋል። የቀድሞው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባል ኬሪያ ኢብራሂም በሰጡት አስተያየት፤ ህገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልል ተተኪ ትውልድን ሆን ብሎ በመዋቅራዊ አሰራር እያጠፋና እያመከነ መሆኑን ገልጸዋል። የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የጥይት ድምፅ በማጥፋት ለክልሉ ሕዝብ ተስፋ የሰጠ ሁነኛ የሰላም በር ቢሆንም፣ ቡድኑ ስምምነቱን ለዳግም ጦርነት ጊዜ መግዣነት በመጠቀም የትግራይ እናቶችን እያስለቀሰ መሆኑን አስገንዝበዋል። የመጀመሪያው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ የነበሩት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት በበኩላቸው፤ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የሰላም ስምምነቱን በማፍረስ በትግራይ ክልል የሰብዓዊ መብት ረገጣውን እያጠናከረ መምጣቱን ገልጸዋል። ቡድኑ ወጣቶችን ለውክልና ጦርነትና ለተለያዩ መማገጃዎች እየተጠቀመባቸው እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ሕዝብን አሸብሮና አስገድዶ ወታደር የማድረግ ዓላማው ከሻዕቢያ የተኮረጀና በአሁኑ ወቅት በስፋት እየተተገበረ ያለ አደገኛ ድርጊት መሆኑን አስረድተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከጋና ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ጋር ተወያዩ
Jul 23, 2026 452
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከጋና ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ጋር በጁብሊ ሀውስ በሁለትዮሽ እና በጋራ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ከአፍሪካ ኅብረት የጤና ዘርፍ ልዩ የመሪዎች የጤና ጉባኤ በተጓዳኝ፣ ከጋና ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ጋር በጁብሊ ሀውስ በሁለትዮሽ እና በጋራ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ከፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ መነሻ ጀምሮ ለዘለቀው ታሪካዊና ጠንካራ የዲፕሎማሲ ግንኙነቷ ትልቅ ሥፍራ ትሰጣለች ሲሉም ገልጸዋል። በአዲስ አበባ የሚገኘው አዲሱ የጋና ኤምባሲ ሕንፃ መጠናቀቅም የሁለቱ አገራት የማይናወጥ ወዳጅነት ምልክት መሆኑን በውይይታችን አንስተናል ነው ያሉት በመልዕክታቸው። ፕሬዝዳንት ማሃማ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነፃነትና የአንድነት አርማነቷን እንደጠበቀች፣ አሁን ደግሞ በአረንጓዴ አሻራና በሌሎች የልማት ዘርፎች እያስመዘገበቻቸው ባሉ አበረታች ለውጦች እና ስኬቶች በእጅጉ መደነቃቸውን ገልጸውልኛል ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ ሀገራችን ለ12ኛ ጊዜ የሚካሄደውን የጣና ፎረም ለማዘጋጀት እያከናወነችው ያለችውን የቅድመ ዝግጅት ስራ የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል ሲሉም ጠቁመዋል። በፎረሙ ቦርድ ላይ እያበረከቱ ላሉት እጅግ የላቀ አመራርም የከበረ ምስጋናችንን አቅርበንላቸዋል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመልዕክታቸው።
ብልፅግና ፓርቲ የሕዝብን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸው ተጨባጭ ለውጦች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jul 22, 2026 413
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ የሕዝብን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸው ተጨባጭ ለውጦች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ በፓርቲና በመንግሥት የተቀናጀ አመራር የስራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋት፣ የገበያ መረጋጋትን ለማረጋገጥና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የጀመራቸው ተጨባጭ ሥራዎች በሕዝብ ሕይወት ላይ የሚታዩ ለውጦችን እያስመዘገቡ መሆናቸውንም ተናግረዋል። አቶ አደም ፋራህ ይህንን የተናገሩት በ2018 በጀት ዓመት በፓርቲና በመንግሥት ቅንጅት በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በገበያ ማረጋጋትና በኑሮ ውድነት ቅነሳ ዙሪያ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት በተገመገመበት መድረክ ማጠቃለያ ላይ ነው። የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የገበያ መረጋጋትና የኑሮ ውድነት ቅነሳ የመንግሥት መደበኛ ፕሮግራሞች ብቻ ሳይሆኑ የፓርቲው ዋና ዋና የፖለቲካ ተልዕኮዎች በመሆናቸው በሁሉም የአመራር እርከኖች በንቅናቄ ተመርተዋል ብለዋል። ይህም ከዕቅድ አፈጻጸም ባለፈ በሕዝቡ የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን አመልክተዋል። በሁሉም ክልሎች በስራ ዕድል ፈጠራና በኑሮ ውድነት ቅነሳ ዘርፎች የሚታዩ መሻሻሎች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ ያለውን የሀገሪቱን አቅምና የሕዝቡን ፍላጎት ከግምት በማስገባት ከዚህ በላይ ሊሠራ የሚገባ ብዙ ሥራ እንዳለ አስገንዝበዋል። ሁለቱንም የትኩረት መስኮች በሕዝብ ንቅናቄ በመምራታችን ጉዳዩን እስከ ቀበሌ ድረስ የአመራር አጀንዳ ማድረግ ችለናል፤ ይህም ተጨባጭ ለውጥ አስገኝቷል ነው ያሉት። አሁን ያለውን ጅምር ማጠናከርና ወደ ከፍተኛ ውጤት ማሸጋገር ይጠበቃል ሲሉም አቶ አደም አስገንዝበዋል። የፓርቲ አደረጃጀቶችና አባላት በዘርፉ ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ በማሳሰብ፣ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ቅንጅት በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል። የእያንዳንዱን አካባቢን የልማት አቅምና የገበያ እውነታ መሠረት በማድረግ ለሕዝቡ ቀጥተኛ ጥቅም የሚያስገኙ ምርቶችን በመለየት የኑሮ ሁኔታን ማሻሻል የቀጣይ ትኩረት መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። እንዲሁም የሕዝብ ባለቤትነትንና የተደራጀ ተሳትፎን በማጠናከር፣ ከአሰራር፣ ከአመለካከትና ከአስተሳሰብ ጋር የተያያዙ ማነቆዎችን በመፍታት ሥራዎቹን ዘላቂ፣ ተቋማዊና ሥርዓታዊ በሆነ አግባብ ማስቀጠል እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዶች በተሻለ አፈጻጸም እንዲተገበሩ ሁሉም የፓርቲ መዋቅሮችና የመንግሥት ተቋማት በቅንጅት፣ በተጠያቂነትና በውጤት ተኮር አሰራር ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ አሳስበዋል። ለሶስት ተከታታይ ቀናት የተካሄደው የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይይት መድረክ፣ በቀጣይ የሕዝብን የኑሮ ሁኔታ የበለጠ ማሻሻል የሚያስችሉ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መጠናቀቁ ተመላክቷል።
ፖለቲካ
ሀገራዊ ምክክር የጋራ አሸናፊነት ማብሰሪያ፤ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ማሳለጫ ነው-የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች
Jul 23, 2026 316
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክር የጋራ አሸናፊነት ማብሰሪያ፤ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ማሳለጫ መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን በማወያየት ምክክር የሚደረግባቸው ስምንት አጀንዳዎችን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም አራት ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምክክር ማድረግ ጀምረዋል። በዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪ አቶ አህመድ ሁሴን ለኢዜአ እንዳሉት፤ ምክክሩ አንዱ የሌላውን ፍላጎት እና አተያይ በአግባቡ እንዲረዳ ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነው። ከዚህ ቀደም ሩቅ ሆኖ በአጀንዳዎች ላይ የግል ምልከታን ማንጸባረቅ የተለመደ ነበር ያሉት አመካካሪው፤ አሁን ግን የሌሎችን ስጋት እና ፍላጎት በደንብ ለማየት ልዩ የሆነ እድል መፈጠሩን አንስተዋል። ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያ አዲስ ባህል እና ልምምድ መሆኑን የገለጹት አቶ አህመድ፤ በምክክር ጉባኤው ለሀገር ግንባታ ገንቢና ጠቃሚ ሀሳቦች እየተነሱበት መሆኑን ጠቁመዋል። የምክክር ጉባኤው አሳታፊ እና አካታች መሆኑ የዜጎችን መተማመን እንደሚያሳድገው ጠቅሰው፤ ይህም ለሀገር መንግሥት ግንባታ እንዲሁም ለሀገር ግንባታ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። ከተመካካሪዎቹ መካከል አቶ መልካሙ ጸጋዬ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም በተቃርኖ ጫፍና ጫፍ ሆነን ስንወጋገዝ ኖረናል ብለዋል።ምክክሩ ለኢትዮጵያ ሁሉም የድርሻውን የሚያበረክትበት አውድ የፈጠረ መሆኑንም ተናግረዋል። በምክክሩ ልማትን ለማፋጠን የሚረዱና የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ሀሳቦች እንደሚፈልቁበት ያላቸውን እምነት ገልጸው፤ ለዚህም እንደ አንድ ተመካካሪ የድርሻዬን ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብለዋል። ምክክር የሁሉ ነገር መፍቻ ቁልፍ በመሆኑ ልዩነትን በኃይል ሳይሆን በምክክር የመፍታት ግብ ይዘን ወደ ምክክሩ መጥተናል ያሉት አቶ መልካሙ፤ የጋራ አሸናፊ የሚያደርገን ይሄው መንገድ ብቻ መሆኑን ገልጸዋለ። ሌላው ተመካካሪ ወጣት ዮሴፍ አበራ በበኩሉ፤ በምክክሩ ላይ በመሳተፌ ብዙ ልምድ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርጉ ሀሳቦች እየመነጩበት መሆኑን መታዘቡን ገልጿል። ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር ወሳኝ እርምጃ ላይ ነን ያለው ወጣት ዮሴፍ፤ ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርግ ሀሳብ ይዘን ተነስተናል እንደሚሳካም ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ ብሏል።
የሃሳብ መቀራረብን በማጠናከር የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ የሚገነባ ምክክር እያደረግን ነው - የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች
Jul 23, 2026 290
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦ በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ያለምንም ገደብ የሃሳብ መቀራረብንና የጋራ መግባባትን በማጎልበት የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ የሚገነባ ምክክር እያደረጉ መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። ከሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች በንዑስ ቡድኖች ተከፋፍለው በተመደቡባቸው አጀንዳዎች ላይ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተመካከሩ ነው። የምክክር ጉባኤው ተመካካሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፣ በኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆዩ ያለመግባባት ጉዳዮችን ለመፍታት በተሰባሰቡ የሕዝብ ወኪሎች እየተካሔደ ያለው ምክክር ለቀጣዩ ትውልድ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ነው። በምክክር ጉባኤው ላይ የሚመከርባቸው አጀንዳዎችም የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋ በማጎልበት ሀገራዊ አንድነትን፣ መከባበርንና ዘላቂ መግባባትን የሚያጠናክሩ እንደሆኑም ገልጸዋል። ተመካካሪ ሊቀ ካህናት መልዓከ ሰላም ጌታሰው በላይ እንዳሉት፤ የምክክር ጉባኤው የሁሉም ዜጎች የሕዝብ ወኪሎች በአንድ መድረክ ተሰባስበው እየመከሩበት የሚገኝ ታሪካዊ ዕድል ነው። ስለ ሀገር አንድነት፣ ሰላምና መግባባት እየመከርን ነው ያሉት ሊቀ ካህናት መልዓከ ሰላም ጌታሰው በላይ፣ በቀጣይም ጠንካራ ሀገራዊ መግባባት እንዲገነባ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ሌላኛው ተመካካሪ ፓስተር ጻዲቁ አብዶ በበኩላቸው፣ ምክክር በኃይማኖታዊ አስተምህሮ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው እሴት መሆኑን ጠቅሰዋል። ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤም ለአሁኑና ለመጪው ትውልድ ጠቃሚ ትምህርት የሚያስተላልፍ የኢትጵያዊያን የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የምክክር ሂደቱ የሐሳብ መሸናነፍ ሳይሆን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የጋራ አሸናፊ ለማድረግ የሚያስችል የመግባባት ሂደት መሆኑንም አመልክተዋል። ተመካካሪ አባገዳ ደቻሳ ወዳጆ በበኩላቸው፣ ምክክሩ ለትውልድ ተስፋ የሚጣልበት ታሪካዊ የተሞክሮ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ሕዝቡም በተስፋ የሚጠብቀው ሂደት በመሆኑ ስለ ኢትዮጵያ ቀጣይ ዕድገትና ልማት በማሰብ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላኛው ተመካካሪ አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ በበኩላቸው፣ በምክክሩ የሕዝብ አጀንዳዎችን በነፃነትና በተገቢው መንገድ የሚያቀርቡበት ምቹ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በዚህም በተመረጡት ዐበይት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ጥልቅና ገንቢ ምክክር እያካሄዱ መሆኑን ገልጸዋል። ለሀገራችን ይጠቅማሉ ብለን በምናምንባቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ወደ መግባባት ለመድረስ እየሠራን ነው ብለዋል። ተመካካሪ አቶ ሳይመን ቶት በበኩላቸው፣ ምክክሩ የመወያየትና የመደማመጥ ባህልን ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፍ ጠንካራ መሠረት በመጣል መግባባት የሰፈነባትን ሀገር ለመገንባት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነት መሰረት የሚጥል ነው
Jul 23, 2026 305
ደሴ ፤ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነት መሰረት የሚጥል መሆኑን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የሐይማኖት አባቶች ገለጹ። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ባሰባሰባቸውና በተለዩ ስምንት አጀንዳዎች ላይ የዋናው የምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የኢትዮጵያን የቆዩ ችግሮች በምክክር በመፍታትና ለሁሉም የምትመች ጠንካራ ሀገር የመገንባት ትልም ተይዞ እየተሰራ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የባቲ ከተማ የሃይማኖት አባት መላከ ፀሐይ ሰምረ አስቻለው እንዳሉት፥ ሀገራዊ ምክክሩ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነትን ለማምጣት መሰረት የሚጥል ነው ። በምክክሩ የመደማመጥ እሴትን በመጠቀምና በማጎልበት ለችግሮች መፍትሄ ማስቀመጥ ይገባል ብለዋል። ለምክክሩ በአጀንዳነት የተመረጡ ጉዳዮችም ችግሮቹን ለመፍታት መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ጠቁመው፥ለጉባኤው ስኬት ሁሉም ሀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ መክረዋል። ሌላው የሰንበቴ ከተማ የሐይማኖት አባት ሸህ ኡመር ሸህ መሀመድ በበኩላቸው፣ የምክክር ኮሚሽኑ እየሄደበት ያለው እርቀት በኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ስኬት ነው ብለዋል። በምክክሩ የሚነሱ ችግሮች መፍትሔ የሚያገኙበት ከመሆኑ ባለፈ ለመጪው ትውልድ ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለማስተላለፍ የሚያግዝ እንደሚሆን ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው በተለዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ መፍትሄ በማምጣት የሕዝቦችን አብሮነት ያጠናክራል ብለው ተስፋ ማድረጋቸውን የሀይማኖት አባቶቹ አመላክተዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ነው-ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
Jul 23, 2026 396
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሂደት በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ዋናውን የምክክር ጉባኤ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፣ ምክክሩ አጀንዳዎችን በማብላላትና በምሁራን ገለጻዎች ተደግፎ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል። ባለፉት ቀናት በተከናወኑ የምክክር መድረኮች ተመካካሪዎች በቡድን ተከፋፍለው የተሰጧቸውን አጀንዳዎች በጥልቀት በማብላላት፣በመደማመጥና በመከባበር ወደ ሐሳብ ማጠናቀር ሂደት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል። ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው የምክክር ጉባኤም ተመካካሪዎች በ50 እና በ10 አባላት በመከፋፈል የመጀመሪያውን የሐሳብ ማመንጨትና ማጠናከር ሂደት ማከናወናቸውን ተናግረዋል። በ10 አባላት በመደራጀት የተካሄደው ውይይት በተመካካሪዎች መካከል የልብ ቅርርብ በመፍጠር እንዲተዋወቁና በተሰጧቸው አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት እንዲመክሩ ማስቻሉን አስረድተዋል። በዚህም ሂደት ተመካካሪዎች እርስ በእርሳቸው እንዲቀራረቡና አጀንዳዎችን በጥራት እንዲያብላሉ በተዘረጋው አሠራር መሠረት ውጤታማ ሥራ መሠራቱን አመልክተዋል። 10 አባላት ባሏቸው ቡድኖች በተካሄደው ምክክር የተጠናቀሩ ሪፖርቶች ላይ ከነገ ጀምሮ 50 አባላት ባሏቸው ቡድኖች በመሰባሰብ ውይይት እንደሚጀመር አስታውቀዋል። በዛሬው ዕለትም ሙያተኞች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በስምንት ቡድኖች ለተከፋፈሉ ተመካካሪዎች ሰፊ ማብራሪያዎችንና መረጃዎችን መስጠታቸውን ገልጸዋል። በሀገር ግንባታ፣ በታሪክ፣ በፌዴራሊዝምና በማንነት ጉዳዮች ላይ በቂ እውቀትና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች ለተመካካሪዎች ልዩ ግብዓት የሚሆን ገለጻ በማቅረብ፣ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ መስጠታቸውን አስረድተዋል። ከነገ ጀምሮም 10 አባላት ባሏቸው ቡድኖች በተካሄደው ምክክር ያጠናቀሯቸውን ሪፖርቶች ለ50 አባላት ባሏቸው ቡድኖች በማቅረብ የቀጣዩ የውይይት ሂደት እንደሚጀመር ገልጸዋል። በምክክር ጉባኤው 4 ሺህ ተመካካሪዎችን ማስተናገድ ሰፊ ዝግጅት የሚጠይቅ ቢሆንም፣ የጤና፣ የጸጥታና ደህንነት፣ እንዲሁም የትራንስፖርት ተቋማት እያደረጉት ያለውን የተቀናጀ ድጋፍ አድንቀዋል። የተከናወኑት የውይይት ሂደቶች በስምንቱም ቡድኖች ውስጥ በ500 ተሳታፊዎች ተደራጅተው ሲካሄዱ ቆይቷል ብለዋል። ከነገ ጀምሮ 50 አባላት ያሏቸው ቡድኖች ያጠናከሯቸውን ሪፖርቶች ለቡድኖቻቸው በማቅረብ ወደ 250 አባላት ባሏቸው ሃምሳ ቡድኖች የሚደረገው ቀጣይ የውይይት ሂደት እንደሚሸጋገር ገልጸዋል። በቀጣይ ሳምንት ደግሞ 4 ሺህ ተሳታፊዎች በ16 ቦታዎች ተከፋፍለው የምክክር ሂደቱን እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል። በውይይቱ ወቅት ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ተሳታፊዎች በፌዴራልና በክልል ሆስፒታሎች ተገቢውን የሕክምና አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም የጸጥታና ደህንነት፣ የትራንስፖርትና ሌሎች ድጋፍ ሰጪ ተቋማት ለተሳታፊዎች አስፈላጊውን አገልግሎት በተቀናጀ መልኩ እየሰጡ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ስር የሰደዱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል ምክክር እያደረግን ነው
Jul 23, 2026 344
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ምክክሩ ስር የሰደዱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የተሻለች አገር ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችል ምክክር እያደረግን ነው ሲሉ በምክክሩ በመሳተፍ ላይ የሚገኙ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ማህበረሰብ አባላት ገለፁ። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክክር የሚደረግባቸውን ስምንት አጀንዳዎች ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በአጀንዳዎቹ ላይም 4 ሺህ ተመካካሪዎች በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ምክክር ማድረግ ጀምረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጰያዊያን እንዳሉትም፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ግልጽና ተስፋ ሰጪ በሆነ መንገድ እየተካሄደ ነው። ምክክሩ የመደማመጥና የጋራ መግባባት ባህልን በማጠናከር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ዕድል መሆኑንም ጠቅሰዋል። ከተመካካሪዎች መካከል አገርነሽ ሃይሌ በሰጡት አስተያየት፤ የምክክር ሂደቱ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ፣ አካል ጉዳተኞችን፣ ሴቶችን፣ ወጣቶችን እና ሌሎችንም የህብረተሰብ ክፍሎች ማካተቱ እጅግ አሳታፊ እንዲሆን አድርጎታል ብለዋል። ለምክክር ሒደቱ ስኬታማነት የድርሻቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት በንቃት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም እና ልማት ቅድሚያ በመስጠት በምክክር ሂደቱ ስኬታማነት አዎንታዊ ሚናችንን መጫወት ይኖርብናል ብለዋል፡፡ ተመካካሪ ወይዘሮ ፎዚያ ሁሴን በበኩላቸው፤ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተርፉ አጀንዳዎች ላይ እየተወያየን በመሆናችን ነገን በሚያሻግር መልኩ የተሰጠንን አደራ በከፍተኛ ኃላፊነት እንወጣለን ብለዋል፡፡ ሁላችንም የተሰጠንን ይህንን ታሪካዊ አደራ በከፍተኛ ኃላፊነት በመወጣት፣ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም እና አንድነት በጋራ መቆም አለብን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ህገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልልን ሕዝብና ተተኪውን ትውልድ ለከፋ አደጋና ጉስቁልና እየዳረገ ነው
Jul 23, 2026 433
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይን ሕዝብና ተተኪውን ትውልድ ለከፋ አደጋና ጉስቁልና እያዳረገ መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የቀድሞ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። የትግራይ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ትዴፓ) ሊቀ-መንበር አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ህገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን ከተመሠረተበት ማግሥት ጀምሮ ችግሮችን በጠመንጃ አፈሙዝ ለመፍታት የሚሞክር ግትር አቋም ያለው የወንጀለኞች ስብስብ ነው። በፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በተገቢው መንገድ ተግባራዊ እንዳይሆን እንቅፋት ሲፈጥር የቆየው ህገወጥ ቡድኑ፤ በአሁኑ ወቅት ሰላማዊ የፖለቲካ አማራጮችን በመዝጋትና ከሻዕቢያ ጋር ያልተቀደሰ ጥምረት በመፍጠር የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር በመፈንቅለ መንግሥት ማፍረሱንም አክለዋል። በተጨማሪም ወጣቶችንና ሕፃናትን ከቤተሰቦቻቸው በመንጠቅ ወደ ጦር ካምፕ በማስገባት ለተለያዩ አካላት የገቢ ምንጭ እያደረጋቸው ይገኛል ብለዋል። የፌዴራል መንግስት ለህገ-ወጡ ቡድን የሚያቀርበው ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ እና የሚያሳየው ትዕግሥት የሕዝቡን ጉስቁልና ለማስቀረት ያለመ መሆኑን አንስተዋል፡፡ የትግራይ ክልል የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር እና የዓረና ሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ገብሩ አስራት በበኩላቸው፤ ህገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን ሻዕቢያን ጨምሮ ከተለያዩ ህገ-ወጥ ኃይሎች ጋር በመጣመር የትግራይን ሕዝብ ለከፋ ጉዳት የሚዳርግ የጥፋት ተግባር ላይ በመሰማራት ጠላትነቱን በተጨባጭ ማረጋገጡን ተናግረዋል። ቡድኑ ለሥልጣን ሲል ከክልሉ ሕዝብ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመተባበር ለሌላ ግጭት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ሻዕቢያ የትግራይን ሕዝብ ለማጥፋት የሚጥር መሆኑን ቀደም ሲል በክልሉ የፈጸመው ጭፍጨፋና ያስከተለው ውድመት ማረጋገጫ ነው ብለዋል። የቀድሞው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የስምረት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባል ኬሪያ ኢብራሂም በሰጡት አስተያየት፤ ህገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ክልል ተተኪ ትውልድን ሆን ብሎ በመዋቅራዊ አሰራር እያጠፋና እያመከነ መሆኑን ገልጸዋል። የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የጥይት ድምፅ በማጥፋት ለክልሉ ሕዝብ ተስፋ የሰጠ ሁነኛ የሰላም በር ቢሆንም፣ ቡድኑ ስምምነቱን ለዳግም ጦርነት ጊዜ መግዣነት በመጠቀም የትግራይ እናቶችን እያስለቀሰ መሆኑን አስገንዝበዋል። የመጀመሪያው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ የነበሩት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት በበኩላቸው፤ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የሰላም ስምምነቱን በማፍረስ በትግራይ ክልል የሰብዓዊ መብት ረገጣውን እያጠናከረ መምጣቱን ገልጸዋል። ቡድኑ ወጣቶችን ለውክልና ጦርነትና ለተለያዩ መማገጃዎች እየተጠቀመባቸው እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ሕዝብን አሸብሮና አስገድዶ ወታደር የማድረግ ዓላማው ከሻዕቢያ የተኮረጀና በአሁኑ ወቅት በስፋት እየተተገበረ ያለ አደገኛ ድርጊት መሆኑን አስረድተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከጋና ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ጋር ተወያዩ
Jul 23, 2026 452
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከጋና ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ጋር በጁብሊ ሀውስ በሁለትዮሽ እና በጋራ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ከአፍሪካ ኅብረት የጤና ዘርፍ ልዩ የመሪዎች የጤና ጉባኤ በተጓዳኝ፣ ከጋና ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ጋር በጁብሊ ሀውስ በሁለትዮሽ እና በጋራ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ከፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ መነሻ ጀምሮ ለዘለቀው ታሪካዊና ጠንካራ የዲፕሎማሲ ግንኙነቷ ትልቅ ሥፍራ ትሰጣለች ሲሉም ገልጸዋል። በአዲስ አበባ የሚገኘው አዲሱ የጋና ኤምባሲ ሕንፃ መጠናቀቅም የሁለቱ አገራት የማይናወጥ ወዳጅነት ምልክት መሆኑን በውይይታችን አንስተናል ነው ያሉት በመልዕክታቸው። ፕሬዝዳንት ማሃማ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነፃነትና የአንድነት አርማነቷን እንደጠበቀች፣ አሁን ደግሞ በአረንጓዴ አሻራና በሌሎች የልማት ዘርፎች እያስመዘገበቻቸው ባሉ አበረታች ለውጦች እና ስኬቶች በእጅጉ መደነቃቸውን ገልጸውልኛል ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ ሀገራችን ለ12ኛ ጊዜ የሚካሄደውን የጣና ፎረም ለማዘጋጀት እያከናወነችው ያለችውን የቅድመ ዝግጅት ስራ የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል ሲሉም ጠቁመዋል። በፎረሙ ቦርድ ላይ እያበረከቱ ላሉት እጅግ የላቀ አመራርም የከበረ ምስጋናችንን አቅርበንላቸዋል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመልዕክታቸው።
ብልፅግና ፓርቲ የሕዝብን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸው ተጨባጭ ለውጦች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jul 22, 2026 413
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ብልፅግና ፓርቲ የሕዝብን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸው ተጨባጭ ለውጦች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ በፓርቲና በመንግሥት የተቀናጀ አመራር የስራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋት፣ የገበያ መረጋጋትን ለማረጋገጥና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የጀመራቸው ተጨባጭ ሥራዎች በሕዝብ ሕይወት ላይ የሚታዩ ለውጦችን እያስመዘገቡ መሆናቸውንም ተናግረዋል። አቶ አደም ፋራህ ይህንን የተናገሩት በ2018 በጀት ዓመት በፓርቲና በመንግሥት ቅንጅት በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በገበያ ማረጋጋትና በኑሮ ውድነት ቅነሳ ዙሪያ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት በተገመገመበት መድረክ ማጠቃለያ ላይ ነው። የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የገበያ መረጋጋትና የኑሮ ውድነት ቅነሳ የመንግሥት መደበኛ ፕሮግራሞች ብቻ ሳይሆኑ የፓርቲው ዋና ዋና የፖለቲካ ተልዕኮዎች በመሆናቸው በሁሉም የአመራር እርከኖች በንቅናቄ ተመርተዋል ብለዋል። ይህም ከዕቅድ አፈጻጸም ባለፈ በሕዝቡ የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን አመልክተዋል። በሁሉም ክልሎች በስራ ዕድል ፈጠራና በኑሮ ውድነት ቅነሳ ዘርፎች የሚታዩ መሻሻሎች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ ያለውን የሀገሪቱን አቅምና የሕዝቡን ፍላጎት ከግምት በማስገባት ከዚህ በላይ ሊሠራ የሚገባ ብዙ ሥራ እንዳለ አስገንዝበዋል። ሁለቱንም የትኩረት መስኮች በሕዝብ ንቅናቄ በመምራታችን ጉዳዩን እስከ ቀበሌ ድረስ የአመራር አጀንዳ ማድረግ ችለናል፤ ይህም ተጨባጭ ለውጥ አስገኝቷል ነው ያሉት። አሁን ያለውን ጅምር ማጠናከርና ወደ ከፍተኛ ውጤት ማሸጋገር ይጠበቃል ሲሉም አቶ አደም አስገንዝበዋል። የፓርቲ አደረጃጀቶችና አባላት በዘርፉ ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ በማሳሰብ፣ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ቅንጅት በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል። የእያንዳንዱን አካባቢን የልማት አቅምና የገበያ እውነታ መሠረት በማድረግ ለሕዝቡ ቀጥተኛ ጥቅም የሚያስገኙ ምርቶችን በመለየት የኑሮ ሁኔታን ማሻሻል የቀጣይ ትኩረት መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል። እንዲሁም የሕዝብ ባለቤትነትንና የተደራጀ ተሳትፎን በማጠናከር፣ ከአሰራር፣ ከአመለካከትና ከአስተሳሰብ ጋር የተያያዙ ማነቆዎችን በመፍታት ሥራዎቹን ዘላቂ፣ ተቋማዊና ሥርዓታዊ በሆነ አግባብ ማስቀጠል እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዶች በተሻለ አፈጻጸም እንዲተገበሩ ሁሉም የፓርቲ መዋቅሮችና የመንግሥት ተቋማት በቅንጅት፣ በተጠያቂነትና በውጤት ተኮር አሰራር ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ አሳስበዋል። ለሶስት ተከታታይ ቀናት የተካሄደው የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይይት መድረክ፣ በቀጣይ የሕዝብን የኑሮ ሁኔታ የበለጠ ማሻሻል የሚያስችሉ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መጠናቀቁ ተመላክቷል።
ማህበራዊ
ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ ቅርሶችን በመጠበቅ ለሀብት ምንጭነት ለማዋል እየተሰራ ነው
Jul 24, 2026 10
ጎንደር፤ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ጥንታዊ ቅርሶችን በመጠገን፣ በማደስና በዘመናዊ ሥርዓት በመያዝ የሃብት ምንጭ ሆነው እንዲቀጥሉ እየተሰራ ያለው ስራ ውጤታማ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ገለጹ። የባለስልጣኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በጎንደር ከተማ የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ነባር ቅርሶችን በማደስና አዳዲስ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የሀብት ምንጭ የማድረግ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቷቸዋል። በዚህም ቅርሶችን በመጠበቅ፣ በመንከባከብና በማደስ የኢኮኖሚ ምንጭ የማድረግ ፍልስፍናው በተሳካ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የጎንደር አብያተ መንግስታትን፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የጅማ አባጅፋር ቤተ መንግስትን፣ የሐረር ቅርሶችንና የነቀምት የቁምሳ ሞረዳ ቤተመንግስት እድሳት ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም በዋና ዋና የቅርስ መገኛ አካባቢዎች ሙዚየሞችን በማስገንባት እና ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን ለጎብኝዎች ክፍት በማድረግ የሀብት ምንጭ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። የአዝማሪ ጨዋታዎችን ጨምሮ የሀገር ባህል ዘፈኖችና ጭፈራዎችን ወደ አደባባይ በማውጣት የገጠሩን ቱሪዝ ልማት በማሳደግ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የጎንደር ከተማ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ማርያም ካሳሁን እንደገለጹት፣ በከተማዋ የተከናወነው የኮሪደር ልማትና የታሪካዊ አብያተ መንግስታት እድሳት የቱሪዝሙ ዘርፉን እንዲነቃቃ አድርጓል። በዚህም በ2017 በጀት ዓመት አንድ ሺህ 914 የነበረው የውጭ ሀገር ቱሪስቶች ቁጥር በ2018 በጀት ዓመት ወደ ስድስት ሺህ 420 ማደግ መቻሉን በማሳያነት አቅርበዋል። ባለስልጣኑም በጎንደር ከተማ ለሚገኘው የደብረ ብርሃን ሥላሴ ጥገና በመጀመሪያው ምእራፍ 30 ሚሊዮን ብር መመደቡን ጠቁመው ሌሎች ቅርሶችንም ደረጃ በደረጃ እንደሚታደሱ ነው የተናገሩት። ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹ በቅርቡ የታደሰው የፋሲል አብያተ መንግስትን ጨምሮ ሌሎች በከተማዋ የሚገኙ የመስህብ ህብቶችን ጎብኝተዋል።
የበጎ ፈቃድ ነጻ የሕክምና አገልግሎት የጤና አገልግሎትን ለሁሉም ማህበረሰብ ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ ጤናማ ዜጋ ለመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው
Jul 24, 2026 104
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የበጎ ፈቃድ ነጻ የሕክምና አገልግሎት የጤና አገልግሎትን ለሁሉም ማህበረሰብ ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ ብቁና ጤናማ ዜጋ ለመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ፡፡ «በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ» በሚል መሪ ሐሳብ የጤና ሚኒስቴር ከቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በጋራ ያዘጋጀው የክረምት የበጎ ፈቃድ የነፃ የጤና ምርመራ፣ ምክርና ሕክምና አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በጉለሌ ክፍለ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወነው የክረምት የበጎ ፈቃድ ሕክምና አገልግሎት ዋና ዓላማ በሽታዎችን ቀድሞ መከላከልና መለየት ላይ ያተኮረ ነው። ይህ አገልግሎት ዜጎች ቀድመው ሕክምና የሚያገኙበት ትልቅ ዕድል መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ዶክተር አብረሃም እሸቴ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በየዓመቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንደሚያካሂድ ጠቁመዋል። በዘንድሮው የክረምት መርሃ ግብርም ከ120ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተለያዩ ነፃ የሕክምና አገልግሎቶችን ለማቅረብ መታቀዱን ገልጸዋል። አገልግሎቱም ከተለመዱት መደበኛ ምርመራዎች ባሻገር የቀዶ ሕክምና፣ የስፔሻሊቲ ሕክምናዎች እንዲሁም እንደ ሲቲ ስካን (CT Scan) እና ኤም አር አይ (MRI) ያሉ የላቁ የዲያግኖስቲክ ምርመራዎችን ያካተተ መሆኑን አስረድተዋል። የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ከሕክምና ሥራዎች ጎን ለጎን በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን መተከል፣ የአቅመ ደካሞች ቤቶችን ማደስ፣ ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግና የማዕድ ማጋራትን እንደሚያካተት ተጠቅሷል፡፡
ኢትዮጵያ በመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤና ወረርሽኞችን በመከላከል ለአፍሪካ ተምሳሌት የሚሆን አቅም ገንብታለች
Jul 24, 2026 105
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ በወረርሽኞች መከላከልና ለአደጋዎች አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተምሳሌት የሚሆን ጠንካራ አቅም መገንባቷን የዓለም ጤና ድርጅት ገለጸ። የአፍሪካ ሀገራት የማይበገር የጤና ስርዓት ለመገንባት በመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ በሰው ሀይል አቅም ግንባታና በዘላቂ የጤና ኢንቨስትመንት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርቧል። በኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ ህብረት እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እያከናወነቻቸው የሚገኙ ተግባራት ሀገሪቱ በዘርፉ ለዓለም ተጨማሪ አበርክቶ እንዳላት የሚያሳዩ ናቸው። በጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም አማካኝነት የእናቶችና የሕጻናት ሞትን በመቀነስ የተገኘው ውጤት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ እንደሚሆንም ጠቅሰዋል። በዚህም የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያን በመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ የልህቀት ማዕከልነት እውቅና ለመስጠት ሂደት መጀመሩን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትም በላቦራቶሪ አቅም፣ በዲጂታል የወረርሽኝ ክትትል፣ በሰው ሀይል አቅም ግንባታና በአደጋ ምላሽ አሰጣጥ በአፍሪካ ካሉ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት አንዱ መሆኑን ተናግረዋል። የዓለም ጤና ድርጅት በቀጣይ ከሕክምና አገልግሎት ባለፈ በበሽታ መከላከል ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ገልጸው፤ የአካባቢ ጥበቃና ፅዳት አገልግሎትን ማሻሻል ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ መሆናቸውንም አመልክተዋል። በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ፣ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ልማት መርሃግብሮችን በመተግበር የከተሞችን ገጽታ ከማስዋብ ባለፈ የህዝብ ጤናን ለማሻሻል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ዲጂታል ጤና ለበሽታዎች ቅድመ ትንበያ፣ ለጤና ዕቅድ ዝግጅትና ለአገልግሎት አሰጣጥ መዘመን ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል። የዓለም ጤና ድርጅትም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ሀገሪቱ የዲጂታል ጤና እያከናወነችው ያለውን ተግባር ለማጠናከር እንደሚሰራ አመልክተዋል። የአፍሪካ ሀገራት የመቋቋም አቅም ያለው የጤና ስርዓት ለመገንባት በመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ በሰው ሀይል አቅም ግንባታ፣ በተቀናጀ ሪፈራል ሥርዓትና በዘላቂ የጤና ኢንቨስትመንት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ምክረ ሃሳብ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ከ1947 ጀምሮ የዓለም ጤና ድርጅት መስራች አባል በመሆን በዓለም አቀፍ የጤና ፖሊሲዎች ቀረጻ ላይ ከ79 ዓመታት በላይ አስተዋጽኦ ስታደርግ ቆይታለች።
በዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመሳተፋችን ታላቅ የዜግነት ኩራት ይሰማናል-በጎ ፈቃደኞች
Jul 24, 2026 74
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የነገ ዕጣ ፋንታን በጋራ በሚቀርጸው ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመሳተፋቸው ታላቅ የዜግነት ኩራት እንደሚሰማቸው ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ የዋናው የምክክር ጉባኤ በጎ ፈቃደኞች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መከፈቱ ይታወሳል። ለዘመናት የዘለቁ ልዩነቶችን በውይይትና በመግባባት ለመፍታት የተጀመረው ይህ ሂደት ለትውልድ የሚተላለፍ አኩሪ ሀገራዊ አሻራ እንደሚሆንም ይጠበቃል። ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የተውጣጡ ዜጎች በንቃት በሚሳተፉበት በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ፣ የስነ-ስርዓት ማስተባበር፣ የተሳታፊዎች መረጃ አገልግሎት፣ ድጋፍና አጠቃላይ የአስተናጋጅነት ሥራዎችን በበጎ ፈቃድ የሚያከናውኑ ወጣቶች የሂደቱ የማይታይ ግን ወሳኝ አካል ሆነዋል። በጎ ፈቃደኛ አቶ ዮሐንስ ግርማ ለኢዜአ እንደተናገሩት፣ ሀገርን በሚመለከት ታሪካዊ ሂደት ውስጥ በፈቃደኝነት ማገልገል ከፍተኛ ኩራትን የሚፈጥር ነው። ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ከሚለው አስተሳሰብ ይልቅ እኔ ለሀገሬ ምን አበረከትኩ ወደሚለው የዜግነት ኃላፊነት መሸጋገር ትልቅ የውስጥ እርካታን እንደሚሰጥና የጋራ ኃላፊነትን እንደሚያጠናክር ጠቁመዋል። እንደ እሳቸው ገለጻ፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሀገር ፍቅርን በተግባር የሚያሳይ ከፍተኛ የዜግነት መገለጫ ነው። በጎ ፈቃደኛ መቅደስ መዝገቡ በበኩላቸው፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሰብአዊነት ከፍተኛ እሴት መገለጫ መሆኑን ጠቅሰው፣ በዚህ ወሳኝ ሀገራዊ ምክክር ሂደት ህዝብንና ሀገርን ማገልገል የሚፈጥረው ስሜት እጅግ ልዩ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ልዩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተመካካሪዎች ተገቢውን እገዛ በማድረግ፣ የመረጃ አገልግሎት በመስጠት እና የጉባኤው ሂደት በተሳለጠ ሁኔታ እንዲካሄድ ድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን አስረድተዋል። ከአፋር ክልል የመጡት በጎ ፈቃደኛ አህመድ አለዉ በበኩላቸው፣ በዚህ ታላቅ ሀገራዊ ኩነት እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ኃላፊነታቸውን መወጣታቸው ከፍተኛ ኩራት እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ በዜጎች መካከል መተማመንን በማጠናከር፣ ዘላቂ ሰላምን በማስፈንና የኢትዮጵያን የጋራ የወደፊት ራዕይ በመቅረጽ ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው እምነታቸውን ገልጸዋል። በጎ ፈቃደኞቹ የሀገራዊ ምክክር የኢትዮጵያን የነገ ዕጣ ፈንታ በጋራ ባለቤትነት የሚቀርጽ ታሪካዊ አጋጣሚ በመሆኑ፣ የዚህ ሂደት አካል መሆናቸው ለሕይወታቸው የማይረሳ ትዝታና ለሀገራቸው የሚያበረክቱት ታላቅ አሻራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
በተያዘው የክረምት ወቅት ከ256 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል
Jul 24, 2026 93
ባህር ዳር ሃምሌ 17/2018;-በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በተያዘው የክረምት ወቅት ከ256 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ አንዱዓለም አያሌው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተያዘው የመኸር ወቅት ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ ነው። በአጠቃላይ በተያዘው መኸር የምርት ዘመንም 412 ሺህ 480 ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን ከ17 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ለማምረት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል። በመኸር እርሻው ከ187 ሺህ በላይ የዞኑ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ ሲሆን እስካሁን ባለው 256 ሺህ 249 ሄክታር መሬት በቆሎ ፣ ጤፍ ፣ ዳጉ ሳ፣ ስንዴ ፣ ሰሊጥ ፣ ሩዝ ፣ አኩሪ አተርና ሌሎች ሰብሎች በዘር መሸፈን ተችሏል። በዘር ከተሸፈነው መሬት ውስጥም ከ169 ሺህ 790 ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም የተዘራ መሆኑን አስረድተዋል። በዞኑ ገበያ ተኮር የሆኑ የቅባት ሰብሎችን በማምረት ለኢንዱስትሪ ግብአትና ለገበያ ለማቅረብ እንዲቻል እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ምርታማነትን ለማሳደግም ለተያዘው እቅድ ስኬትም 484 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያና ከ28 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት ተችሏል ብለዋል። የተሰራጨው የምርጥ ዘርና ማዳበሪያ በዞኑ ባለፈው በጀት ዓመት በሔክታር የተገኝውን 41 ኩንታል ምርት ወደ 43 ነጥብ ስምንት በመቶ ለማሳደግ የሚያስቸል ነው ብለዋል። እቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካትም ከዞን እስከ ቀበሌ ያለው አመራርና ባለሙያ ለአርሶ አደሩ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ አመላክተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምግብ ሉዓላዊነትንና የኢንዱስትሪ ግብአትን መሰረት ያደረጉ የግብርና ልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው
Jul 24, 2026 97
አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምግብ ሉዓላዊነትንና የኢንዱስትሪ ግብአትን መሰረት ያደረጉ የግብርና ልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ውጤትም እየተመዘገበ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የክልሉን መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የልማት ኢንሼቲቮች እየተተገበሩ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴ ልማት እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተፈጥሮ ሃብት ልማት ባለፈ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ሂደት የተመዘገበውን ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በመሆኑም የምግብ ሉዓላዊነትንና የኢንዱስትሪ ግብአትን መሰረት ያደረጉ የግብርና ልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ውጤትም እየተመዘገበባቸው ይገኛል ብለዋል። በቱሪዝም እና የማዕድን ሃብት ልማት፣ መስኖ ልማትና በኩታ ገጠም እርሻ፣ የሌማት ትሩፋት እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት አስደናቂ ስኬት መመዝገቡን ጠቅሰዋል።
በሲዳማ ክልል በበልግ እርሻ ተዘርተው የደረሱ ሰብሎችን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው
Jul 24, 2026 71
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በበልግ እርሻ ተዘርተው የደረሱ ሰብሎችን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ የእንክብካቤና የክትትል ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞን ጨምሮ የክልሉ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በበልግ ወቅት በተለያዩ ሰብሎች የለሙ ማሳዎችን እየገበኙ ነው። በጉብኝቱ ወቅት የቢሮው ኃላፊ መምሩ ሞኬ እንዳሉት፤ በሲዳማ ክልል በበልግ እርሻ ተዘርተው የደረሱ ሰብሎችን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ። በክልሉ በበልግ እርሻ በቆሎ፣ ቦሎቄና ሌሎች ሰብሎችን ጨምሮ 152 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ለምቷል ብለዋል፡፡ ከዚህም 24 ሚሊየን ኩንታል ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተው፤ በምርት የተሸፈነውን ማሳ ውጤታማ ለማድረግም የእንክብካቤና የክትትል ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አመልክተዋል፡፡ በበልግ ወቅት የመስኖና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም የለማው ሰብል የሚጠበቀውን ምርት እንዲሰጥ እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ምክር ቤቱ የህዝቡ የልማት ጥያቄዎች እንዲመለሱ ውጤታማ የክትትልና የቁጥጥር ስራ አከናውኗል
Jul 24, 2026 77
አርባምንጭ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህዝቡ የልማት ጥያቄዎች እንዲመለሱ ውጤታማ የክትትልና የቁጥጥር ስራ ማከናወኑን ገለጸ፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአርባምንጭ ከተማ እያካሄደ ነው። የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወላይቴ ቢቶ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ አካላትን የስራ እንቅስቃሴ በመከታተልና በመቆጣጠር ውጤታማ ተግባር አከናውኗል። የአስፈጻሚ አካላት የልማት እንቅስቃሴን በቋሚ ኮሚቴዎች በማስገምገምና በመስክ ስራ ክትትልና ድጋፍ ጠንካራ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል። በበጀት ዓመቱ በክልሉ ሁለንተናዊ ዕድገት ለማስመዝገብ፣ የህዝቡን የልማት ፍላጎት እንዲሁም ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎችን ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት መደረጉን አንስተዋል ። በተለይም የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እንዲመለሱ የተደረገ ጥረት ውጤታማ መሆኑን አመልክተዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 24, 2026 0
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በመዲናዋ ዘመኑን የዋጁ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት በከተማዋ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታን በለሚ ኩራ ከፍለ ከተማ ተገኝተው በይፋ አስጀምረዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፥ የስማርት ፖሊቴክኒክ ግንባታው ወጣቶችን በክህሎት በማልማት የሀገርን እድገት ለማፋጠን ያለመ ነው ብለዋል። ባለፉት የለውጥ አመታት በመዲናዋ ወጣቶች የክህሎትና የቴክኖሎጂ ልማት ላይ ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል። እነዚህ በክህሎትና በቴክኖሎጂ የበቁ ወጣቶች አሁን ላይ ከራሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው አልፈው በሀገር ሁለንተናዊ እድገት ላይ የበኩላቸውን አሻራ እያሳረፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል። አሁን ላይ ወጣቶችን ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ልክ የማብቃት ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል። አዲሱ ስማርት ፖሊቴክኒክ የጀርመንን የቴክኒክና ሙያ ልምድ መነሻ በማድረግ፣ በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚገነባና ትውልድ ተሻጋሪ እውቀት የሚገበይበት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል። ኮሌጁ ወጣቶች እውቀትን የሚታጠቁበት፣አዕምሮ እና የሚሰሩ እጆች ተጣጥመው ሀሳብ የሚያፈልቁበት መሆኑን ገልጸዋል። ኮሌጁ በአመት በርካታ አዳዲስ ሰልጣኞችን የመቀበል አቅም እንደሚኖረው ጠቁመው፤ በዘመናዊ ማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሙኒኬሽንና በቴክስታይል ቴክኖሎጂ መስኮች ያሰለጥናል ብለዋል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ፣ በጀትና ጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከተማ አስተዳደሩ በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ በበኩላቸው፤ የሚገነባው ኮሌጅ ወጣቶች በስልጠና ወቅት የሚያመጧቸውን የቴክኖሎጂ ሀሳቦችና የምርምር ውጤቶች ወደ ተግባራዊ ቢዝነስ እንዲቀይሩ፣የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ እንዲመሰርቱና ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ አስጀመሩ
Jul 24, 2026 9
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት ከሰዎች ለሰዎች ድርጅት ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ አስጀምረዋል። የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታው ሲጠናቀቅ ወጣቶችን በማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሪክና ኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሙዩኒኬሽንስ፣ በቴክስታይል እና የሲኤንሲ (CNC) ቴክኖሎጂዎች ላይ ተግባር ላይ ያተኮረ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም ሥልጠና እንደሚሰጥ ከንቲባዋ ገልጸዋል። ሀገርን ማልማት እና ከድህነት መላቀቅ በንድፈ ሐሳብ ብቻ በተገደቡ ትምህርቶች ማሳካት ስለማይቻል፣ ሐሳብን የሚያፈልቁ አዕምሮዎችን እና የሚሠሩ እጆችን ያጣመረ ክህሎት መር የሰው ኃይል እጅግ አስፈላጊ መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አመልክተዋል። ዛሬ ያስጀመርነው ፕሮጀክት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ወጣቶቻችንን ከሥራ ፈላጊነት ወደ ሥራ ፈጣሪነት፣ ከንድፈ ሐሳብ ወደ ተግባር የሚያሸጋግር፣ አዲስ የሥራ እድል የሚፈጥር የክህሎት ድልድይ የሚሆን ነው ብለዋል። የዚህ ኮሌጅ ግንባታ በጥራትና በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በልዩ ትኩረት የምንከታተለው ይሆናልም ነው ያሉት። ፕሮጀክቱን በትብብር የሚገነባው የረጅም ጊዜ የልማት አጋር የሆነው ሰዎች ለሰዎች ድርጅት እና የሚሠራው ለትውልድ የሚሻገር ዐሻራ ነው በማለት መሬታቸውን ለፕሮጀክቱ የለቀቁ አርሶ አደሮችንም አመስግነዋል።
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመጪዎቹ ሶስት ዓመታት የላቀ አገልግሎት ለመስጠት የቴክኖሎጂና ዲጂታል መሰረተ ልማት ይገነባል
Jul 24, 2026 107
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመጪዎቹ ሶስት ዓመታት ተቋማዊ አቅምና ዝግጁነትን ለማሳደግ፣ ዜጋ ተኮር የላቀ አገልግሎት ለመስጠት የቴክኖሎጂና ዲጂታል መሰረተ ልማት ለመገንባት ይበልጥ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ አስታወቀ፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት የመንግስት አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ዜጋ-ተኮር ማድረግ የሚያስችል የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድና ፍኖተ ካርታ ይፋ አድርጓል፡፡ ፍኖተ ካርታው የ«ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030» ስትራቴጂን መነሻ በማድረግ፣ የዜጎችን የአገልግሎት ተደራሽነት፣ ጥራትና ቅልጥፍና ማሳደግ የሚያስችሉ ቁልፍ የለውጥ አቅጣጫዎችን አካቷል። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ በመድረኩ እንደገለጹት፤ ፍኖተ ካርታው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በቀጣይ ሶስት ዓመታት ምን ዓይነት የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት መገንባት እንዳለበት በግልጽ የሚያመላክት ሰነድ ነው። የስትራቴጂክ ዕቅዱ መሠረትም መሶብ ባለፈው አንድ ዓመት ያከናወናቸውን ሥራዎች በመገምገም፣ በቀጣይ የሚከናወኑ የዲጂታል ሽግግር፣ የአገልግሎት ጥራት ማሻሻያ እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሥራዎችን የሚመራ ይሆናል ብለዋል። ዕቅዱ ከ«ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030» ራዕይ፣ ከሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም አቅጣጫዎች እና ከሀገራዊ የዲጂታል ልማት ግቦች ጋር ተጣጥሞ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በአገልግሎቱ የእቅድና ፕሮግራም ዳይሬክተር ደሳለኝ ድንገታ ባቀረቡት ጽሁፍ፤ በመሶብ የተዘጋጀው ስትራቴጂያዊ ፍኖተ ካርታ በሶስት ዋና ዋና የትኩረት መስኮች ላይ ያተኮረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም የመጀመሪያው ተቋማዊ አቅምና ዝግጁነትን ማሳደግ መሆኑን ጠቅሰው የመሶብን የመፈጸም አቅም ማጎልበት፣ ዘመናዊ የአፈጻጸም አመራር ሥርዓት መዘርጋት እንዲሁም የሰው ኃይል ብቃትን ማሳደግና ውጤታማ የሥራ ባህል መገንባት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃም ዜጋ ተኮር የላቀ አገልግሎት መስጠት ሲሆን የመሶብ አገልግሎቶችን ተደራሽ፣ ፍትሃዊና ዲጂታል ማድረግ፣ የዲጂታል አገልግሎት አጠቃቀምን ማስፋፋት ብሎም የጥሪ ማዕከል አገልግሎትን ማጠናከርና የተገልጋዮችን እርካታ ማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥርዓቶችን መዘርጋት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በሶሰተኛ ደረጃም የላቀ ቴክኖሎጂና ዲጂታል መሰረተ ልማት መገንባት መሆኑን ጠቅሰው የሳይበር ደህንነትን ማጠናከርና ዘመናዊ የዲጂታል አገልግሎት ሥርዓቶችን ማልማት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ የፍኖተ ካርታው ዝግጅት የተመሠረተው በሀገራዊ የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ፣ በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ማዕቀፍ፣ በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ እንዲሁም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ላይ መሆኑንም አክለዋል፡፡ ዛሬ ይፋ የተደረገው ፍኖተ ካርታ፤ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ ቀልጣፋና ዜጋ ተኮር የመንግስት አገልግሎት ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም ተመላክቷል፡፡
የኢትዮ-ቴሌኮም ቀጣዩ አድማስ ስትራቴጂ በአፍሪካ የዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ የመሪነት ሚና መወጣት የሚያስችል ነው
Jul 23, 2026 284
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮ-ቴሌኮም ቀጣዩ አድማስ ስትራቴጂ በአፍሪካ የዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ የመሪነት ሚና መወጣት የሚያስችል መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ። ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የ2018 በጀት ዓመትና የቀጣዩ አድማስ ስትራቴጂ አፈፃፀም ላይ በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ሰባት ዓመታት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በትጋት ሲሠራ መቆየቱን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት የተጀመረውና ለሦስት ዓመታት የሚተገበረው"ቀጣዩ አድማስ" ስትራቴጂ፣ ሁለንተናዊ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማፋጠን ያለመ መሆኑን አስገንዝበዋል። ስትራቴጂው ተቋሙ በአፍሪካ የዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ የድርሻውን እንዲወጣ ከማስቻሉም በላይ፣ለአፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት ጠንካራ መሠረት የሚጥል መሆኑን ገልጸዋል። በስትራቴጂው የአንድ ዓመት አፈፃፀምም በርካታ የኔትወርክ ማስፋፊያና የማዘመን ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በዚህም 603 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቅሰው፣ ይህም አጠቃላይ የሞባይል ጣቢያዎችን ቁጥር ወደ 10 ሺህ 613 ከፍ ማድረጉን አስታውቀዋል። በተጨማሪም 195 የገጠር ሞባይል ጣቢያዎች መገንባታቸውን ገልጸው፣ በዚህም 117 ወረዳዎች የቴሌኮሙ አገልግሎት ተደራሽ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ይህም የአገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት ዲጂታል አካታችነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት የኔትወርክ ማሻሻያና ማስፋፊያ ሥራዎች በስፋት መከናወናቸውን ጠቅሰው፣ 264 ተጨማሪ ከተሞች የአራተኛ ትውልድ (4ጂ) አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል። በዚህም የ4ጂ ኔትወርክ ሽፋን ያላቸው ከተሞች ቁጥር ወደ 1 ሺህ 200 ከፍ ማለቱን ገልጸዋል። በተጨማሪም ሰባት አዳዲስ ከተሞች የአምስተኛ ትውልድ (5ጂ) አገልግሎት በማግኘታቸው፣ የ5ጂ ተጠቃሚ ከተሞች ቁጥር 33 መድረሱን አስታውቀዋል። ኢትዮ ቴሌኮም በ2018 በጀት ዓመት 215 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ በማስመዝገብ የዕቅዱን 99 ነጥብ 7 በመቶ ማሳካቱንም ገልጸዋል። ይህም ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ33 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። በቴክኖሎጂና በመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎች የተመዘገበውን ውጤት መሠረት በማድረግ፣የኢትዮ ቴሌኮም አጠቃላይ የደንበኞች ቁጥር 90 ነጥብ 1 ሚሊዮን መድረሱን ዋና ሥራ አስፈፃሚዋ ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ 475 አዳዲስና የተሻሻሉ ምርቶችና አገልግሎቶች ለደንበኞች ማቅረብ መቻሉንም ጠቅሰዋል። በተጨማሪም የቴሌብር ተጠቃሚዎች ቁጥር 60 ነጥብ 5 ሚሊዮን መድረሱን አስታውቀዋል።
ስፖርት
የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
Jul 24, 2026 70
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የጀርመን እግር ኳስ ፌዴሬሽን የርገን ክሎፕን የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን ዛሬ ይፋ አድርጓል። የ59 ዓመቱ ጀርመናዊ የአራት ዓመት ውል የተፈራረሙ ሲሆን ስምምነቱ አሰልጣኙን እስከ 2030 የዓለም ዋንጫ መጨረሻ ድረስ የሚያቆያቸው ነው። ክሎፕ በቦታው የተኩት በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ጀርመን በ32ቱ ዙር በፓራጓይ ተሸንፋ ከውድድሩ ውጪ ከሆነች በኋላ ከኃላፊነታቸው የለቀቁትን ጁሊያን ናጌልስማንን በመተካት ነው። ከሊቨርፑል የዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ የሬድ ቡል ሳልስበርግ የዓለም እግር ኳስ ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት ክሎፕ፣ የጀርመን እግር ኳስን እንደገና ወደ ቀደመ ገናናነቱ የመመለስ ትልቅ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ክሎፕ ከጀርመን ብሔራዊ ቡድን ጋር የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም. በዩኤፋ ኔሽንስ ሊግ (Uefa Nations League) ከኔዘርላንድስ ጋር ያደርጋሉ።
የዓለም አትሌቲክስ የአትሌት ትዕግስት አሰፋ የሴቶች ብቻ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን አፀደቀ
Jul 23, 2026 134
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የዓለም አትሌቲክስ የኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ የሴቶች ብቻ (women’s only) የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን ዛሬ ማፅደቁን ይፋ አድርጓል። አትሌት ትዕግስት እ.አ.አ አፕሪል 26 / 2026 በለንደን ማራቶን 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ከ41 ሴኮንድ በመግባት እ.አ.አ በ2025 በራሷ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን በዘጠኝ ሴኮንድ በማሻሻል አሸንፋለች። የዓለም አትሌቲክስ የአትሌቷን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረ ወሰን ዛሬ ማፅደቁን አስታውቋል። የሴቶች ብቻ (women’s only) የዓለም ክብረ ወሰን ሴቶች ብቻ በሮጡበት ውድድር ብቻ የተመዘገበ የዓለም ፈጣን ሰዓት ማለት ነው። የዚህ የዓለም ክብረ ወሰን አመዘጋገብ በሴቶች ውድድር ላይ የወንድ አሯሯጮች ወይም ወንዶች ተቀላቅለው ሲሮጡ (አጠቃላይ ሩጫ) ከሚመዘገበው የዓለም ክብረ ወሰን ጋር የሚለያይ ነው። ወንዶች በሴቶች ውድድር ላይ መኖራቸው የውድድሩን አዝማሚያ እና ሴቶች የሚያስመዘግቡት ሰዓት ላይ ተጽእኖ እንደሚያሳድር የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል። ሴት እና ወንድ ተደባልቀው በሚሮጡበት አጠቃላይ የሴቶች ማራቶን ውድድር የዓለም ክብረ ወሰንን (Overall women's world record) የያዘችው ኬንያዊቷ አትሌት ሩት ቼፕጌቲች ናት። ሩት እ.አ.አ በ2024 በቺካጎ ማራቶን 2 ሰዓት ከ9 ደቂቃ ከ56 ሴኮንድ በመግባት ክብረ ወሰኑን ጨብጣለች። የዓለም አትሌቲክስ ከአትሌት ትዕግስት በተጨማሪ ሰባት የዓለም ክብረ ወሰኖችን ማጽደቁን አስታውቋል። እውቅናና ፈቃድ በተሰጣቸው ውድድሮች ላይ ማሸነፍ፣ የውድድር ሜዳዎቹ የሚፈለገውን መስፈርት ያሟሉ መሆንና አትሌቶች በአበረታች ቅመም ምርምራ ውጤት ጤነኛ መሆናቸው መረጋገጥ አትሌቶች የዓለም ክብረ-ወሰን ባለቤት የሚሆኑባቸው ዋነኛ ቅደመ-ሁኔታዎች ናቸው።
የስፔኑ ሮድሪ የዓለም ዋንጫው ኮከብ ተጫዋች ሆኖ ተመረጠ
Jul 20, 2026 535
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጣምራ አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ዛሬ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ተጠናቋል። በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ ዋንጫውን አንስታለች። ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ የኮከብ ተጫዋቾች ሽልማት ስነ ስርዓት ተካሂዷል። በዚሁ መሰረት የስፔኑ አምበል ሮድሪ የዓለም ዋንጫው ኮከብ ተጫዋች በመባል ተመርጧል። የስፔኑ ተከላካይ ፓዎ ኩባርሲ የወጣት ኮከብ ተጫዋች ሽልማትን አግኝቷል። ኡናይ ሲሞን (ስፔን ) የውድድሩ ኮከብ ግብ ጠባቂ ሆኗል። ፈረንሳዊው ኪሊያን እምባፔ 10 ግቦች በማስቆጠር የኮከብ ግብ አግቢነቱን ሽልማት ወስዷል።
ስፔን አርጀንቲናን በመርታት የዓለም ዋንጫን አነሳች
Jul 20, 2026 397
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ግብ ሳይቆጠርበት በአቻ ውጤት ተጠናቋል። የአርጀንቲና የአማካይ ተጫዋች ኤንዞ ፈርናንዴዝ በ93ኛው ደቂቃ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። በ90 ደቂቃ አሸናፊ ባለመገኘቱ ቡድኖቹ ወደ ጭማሪ ሰዓት አምርቷል። ተቀይሮ የገባው ፌራን ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በጨዋታው ስፔን ፍጹም የበላይነት ወስዳለች። የአርጀንቲናው ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ በርካታ ያለቀላቸው ኳሶችን አድኗል። ተጋጣሚዋ አርጀንቲና በጨዋታው ደካማ እንቅስቃሴ አድርጋለች። ቡድኑ የግብ እድል መፍጠር ተስኖታል። ውጤቱን ተከትሎ ስፔን ለሁለተኛው የዓለም ዋንጫን አንስታለች። አውሮፓዊቷ ሀገር እ.አ.አ በ2010 ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 19ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ እንደነበረች ይታወሳል። አርጀንቲና የዓለም ዋንጫ ክብሯን ማስጠበቅ አልቻለችም። ለአራተኛ ጊዜ ዋንጫ የማንሳት ህልሟ አልተሳካም።
አካባቢ ጥበቃ
አረንጓዴ ዐሻራ የሥነ-ምኅዳር ደህንነትን በማስተካከል ዕድገትን በማፋጠን ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው
Jul 23, 2026 161
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የሥነ-ምኅዳር ደኅንነት በማስተካከል ዕድገትን የሚያፋጥን ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን "ተስፋን እንትከል" መሪ ሃሳብ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ ዳርቻ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። በዚሁ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይም፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልጽግና የሚያረጋግጥ ብሔራዊ የልማት ትልም መሆኑን ገልጸዋል። በዘንድሮው መርሃ ግብር ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ሁሉም የማኅብረሰብ ክፍል በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል። በዚሁ መሠረትም የተለያዩ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ ሠራተኞችና የማኅበረሰብ ክፍሎች በየአካባቢያቸው ችግኝ በመትከል ዐሻራቸውን እያኖሩ ይገኛል። የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አመራርና ሠራተኞችም በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ጎሮ የወንዝ ዳርቻ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። በዚሁ ወቅት የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የሥነ-ምኅዳር ደኅንነት በማጠናከር ዘላቂ ልማትን የሚያፋጥን ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መርሃ ግብሩ በ2011 ዓ.ም ከተጀመረ ወዲህ ባሉት ሰባት ተከታታይ ዓመታት በርካታ ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰዋል። መርሃ ግብሩ የሥነ-ምኅዳር ሚዛንን ከማስጠበቅ ባለፈ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም ዛፍ መትከል ለሰው ልጆች የአዕምሮ እርካታና የልብ ደስታን በመፍጠር ተስፋን የማለምለም አቅም እንዳለው ጠቁመዋል። በተጨማሪም የተተከሉ ችግኞች ፀድቀው ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ መንከባከብና በቀጣይነት መከታተል የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን አሳስበዋል። በመርሃ ግብሩ የተሳተፉት የምክር ቤቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ተረፈ በዳዳ በበኩላቸው፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከሰው ልጆች ሕይወት ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው የልማት ተግባር ነው ብለዋል። በዚህ ብሔራዊ ዘመቻ ላይ በመሳተፍ አሻራ ማኖር፣ በሀገር ልማትና በትውልድ ተስፋ ላይ አሻራ የማኖር ዕድል መሆኑንም ገልጸዋል። ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መሳተፋቸውን የገለፁት ደግሞ ሌላኛዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የመንግሥታት ግንኙነት፣ የብዝኅነትና የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዳይሬክቶሬት ተጠባባቂ ዳይሬክተር መንደሪን ማርቆስ ናቸው። መርሃ ግብሩ ለቀጣዩ ትውልድ ልምላሜን የተላበሰች ኢትዮጵያ ለማስረከብ ያለመ በመሆኑ፣ እስካሁን የተከሏቸውን ችግኞች በመንከባከብ እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ የትራንስፖርት ባለሙያ አቶ ኬኔዲ መላኩ በበኩላቸው፣ ከልጅነት ጀምሮ ችግኝ የመትከል ልምድ እንዳላቸው ገልጸዋል። ይህም ለተፈጥሮ ጥበቃና ለችግኝ እንክብካቤ ያላቸውን ግንዛቤ የበለጠ እንዲጎለብት አስችሎኛል ብለዋል።
የፅዱ ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቭ ከተሞችን ውብ፣ ፅዱ፣ ለኑሮ እና ለቱሪዝም ፍሰት የተመቹ እንዲሆኑ አድርጓል
Jul 23, 2026 198
ባህር ዳር ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡-የፅዱ ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቭ ከተሞችን ውብ፣ ፅዱ ፣ ለኑሮ እና ለቱሪዝም ፍሰት የተመቹ በማድረግ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ማድረጉን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ገለፀ። ''ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ'' በሚል መሪ ሀሳብ የሦስተኛ ዙር ክልል አቀፍ የአካባቢ ብክለት መከላከል ዘመቻ የንቅናቄ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በባህር ዳር ከተማ ተካሂዷል። የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፍሬነሽ መኩሪያ በመድረኩ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚያስችሉ ስራዎች በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ ይገኛል። በተለይ ከለውጡ ዓመታት ወዲህ የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የሚያስችሉ ወሳኝ ፖሊሲዎችን፣ አዋጆችን፣ መመሪያዎችንና ደንቦችን አውጥቶ በመተግበር ውጤታማ ስራ ማከናወን መቻሉን ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅትም በከተሞች በስፋት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት፣የአረንጓዴ አሻራና መሰል የልማት ስራዎች ለፅዱ ኢትዮጵያ መጠናከር ሰፊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም በሃይቆች፣ ወንዞችና ሌሎች የውሃ አካላት ብሎም በመኖሪያ አካባቢዎች ለማሕበረሰቡ ጤና አደገኛ የሆኑ የፕላስቲክ ውጤቶችን በማስወገድ በኩል ምሳሌ የሚሆን ስራ መሰራቱን አረጋግጠዋል። መንግስት የአካባቢ ጥበቃን ለዘላቂ ልማትና መጭውን ትውልድ ታሳቢ በማድረግ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለበለጠ ውጤታማነት በተሻለ ትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ''ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ'' ሦስተኛው ዙር ንቅናቄ የፕላስቲክ ውጤቶችን በማስወገድ፣ የድምፅ ብክለትን በመከላከል እና የብዝሃ ህይወት መመናመን እና የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል በሚያስችሉ ተግባራት ላይ ህብረተሰቡን እያሳተፈ ይገኛል። የአማራ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ኃላፊ አቶ በልስቲ ፈጠነ በበኩላቸው፤ በፅዱ ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቨ በርካታ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን ተችሏል። በተለይም ጣና ሀይቅንና ሌሎች የውሃ አካላትን ከፕላስቲክ ቆሻሻና ሌሎች በካይ ነገሮች በማፅዳት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ነው ያሉት። አሁን ላይ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመሰብሰብና መልሶ መጠቀም የሀብት መፍጠሪያ መሆኑን አመልክተው ፤የአካባቢ ብክለትን በዘላቂነት በመከላከል ምቹ የኑሮ አካባቢ በመፋጠር የተጀመሩ ስራዎች ተጠናከረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። መንግስት በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ከሀገር አልፎ ለአህጉርና ዓለም አቀፋ መድረክ ምሳሌ የሚሆን ስራ እየሰራ ነው ያሉት ደግሞ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ አቶ ይትባረክ አወቀ ናቸው። በፅዱ ኢትዮጵያ ከተሞችን በመግለጥና ለቱሪዝም ዘርፉ ማደግ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅስው ይህ ንቅናቄም በተገቢው መንገድ እንዲተገበርና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል። በመድረኩ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና ከተማ አስተዳደር አመራሮችና ባለሙያዎች ብሎም ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን በባህር ዳር ከተማ የፅዳት ዘመቻና የፓናል ውይይት ተከናውኗል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ከመትከል ባሻገር ለትውልድ የሚተርፍ አርዓያነት ያለው ተግባር ነው
Jul 23, 2026 154
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ከመትከል ባሻገር ለትውልድ የሚተርፍ አርዓያነት ያለው ተግባር መሆኑን የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀይማኖት ዘለቀ ገለጹ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ የዘንድሮውን የክረምት አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በቤላ 18 ቀበሌ የወንዝ ዳርቻ አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሀይማኖት ዘለቀ፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ከመትከል ባለፈ ለመጪው ትውልድ ታሪክ የምናኖርበት አርአያነት ያለው ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። የችግኝ ተከላው የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥን ከመቋቋም እና የግብርና ምርታማነትን ከማሻሻል አንጻር ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ እንዳለውም ተናግረዋል። በመሆኑም ትኩረታችን ችግኝ መትከል ላይ ብቻ ሳይወሰን፤ የተተከሉትን በማሳደግ፣ በመንከባከብ እና የፅድቀት መጠናቸውን በማረጋገጥ ላይ ሊሆን ይገባል ሲሉም አሳስበዋል። መርሃ ግብሩ ለምግብ ዋስትና የሚረዱ የፍራፍሬ እና ለአካባቢ ጥበቃ ጠቀሜታ ያላቸው የዛፍ ዝርያዎችን ያካተተ መሆኑንም ገልጸዋል። መገናኛ ብዙሃን መረጃን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ሀገራዊ የደን ሽፋን ጥረትን ለመደገፍ ያላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ባለሥልጣኑ በ8ኛው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 45 ሺህ 125 ችግኞችን ለመትከል አቅዶ እየሰራ ሲሆን፣ እስካሁን በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች ከ43 ሺህ በላይ ችግኞች መተከላቸው ተገልጿል።
ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የእንጦጦ - ቀበናን የወንዝ እና የወንዝ ዳር ፕሮጀክት ጎበኙ
Jul 23, 2026 231
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦የብልፅግና ፓርቲ ዋናው ማዕከል እና የክልል ቅ/ፅህፈት ቤት በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች በመዲናዋ በመፍጠር እና በመፍጠን የተገነቡ የወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክቶችን ተዟዙረዉ ጎብኝተዋል። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዋናው ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ እና ሌሎችም የፌዴራል፣ የአዲስ አበባ እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በጉብኝቱ ተሳትፈዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የብልፅግና ፓርቲ ምናብ ወደ ውጤት እየተቀየረባት የምትገኘው ውቧ መዲናችን ሁሌም አዲስ እየሆነች ትገኘለች ብለዋል። አዲስ አበባ የብልፅግና አይቀሬነት ማሳያ መሆኗን የገለፁት ከንቲባ አዳነች ተግተን በመሥራት በላቁ አዳዲስ ድሎች እንገናኛለን ብለዋል። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ በበኩላቸው፤ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች የከተማዋን ገፅታ ከመገንባታቸው ባሻገር የሕዝቡን የኑሮ ደረጃ ከፍ ማድረጋቸውን አስረድተዋል። ከፍተኛ አመራሮች 10.5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውን፣ አረንጓዴ ቦታዎች፣ የህፃናት መጫወቻዎች፣ የወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ ሱቆች፣ ካፍቴሪያዎች፣ ቤተ መፅሀፍት ፣ የከተማዋ ነዋሪ አንዱ የመዝናኛ ማዕከል የሆነውን የቀበና ግድብ እና ሌሎችም የህዝብ መገልገያዎች ያሉትን የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ ዳር ፕሮጀክትን ተዟዙረዉ መጎብኘታቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 20318
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 13182
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 11974
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 11876
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የአረንጓዴ ዐሻራ፤ ከሥነ-ምኅዳር ዘብ እስከ ዓለም የልማት ተምሳሌት
Jul 23, 2026 329
በመጽሔት አንለይ በወሳኝ ሀገራዊ የልማት ውይይቶች ላይ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸው፣ በዚህም በርካታ ሚሊየን ሄክታር መሬት መታደሱ እንዲሁም የተመዘገበ የደን ሽፋን በአበይት ጉዳይነት ይነሳሉ። ኢትዮጵያ እየተገበረችው ባለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የአርሶ አደሩ ምርታማነት ማደግ፣ የወጣቱ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን፣ የእናቶች የኑሮ መሻሻልና የተፈጥሮ ሃብት መጠበቅ መቻሉ እንዲሁም የአየር ንብረት መዛባትን ማስተካከልና የደን ሽፋንን ማሳደጉ ለመርሃ ግብሩ ውጤታማነት በአብነትነት ይጠቀሳሉ። በዚህ አተያይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተራ የችግኝ ተከላ ዘመቻ ባሻገር በአካባቢ ጥበቃ፣ በግብርና፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ልማት ዘርፎች መዋቅራዊ ለውጥ በማምጣት አንጸባራቂ ውጤት እያሰገኘ ነው። የዓለም አየር ንብረት ጉዳይ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ባለበት ወቅት፣ አፍሪካ የችግሩ ተጠቂ ብቻ ሳትሆን ለመፍትሄውም የራሷን ልምድና አቅም ማበርከት እንደምትችል እያሳየች ይገኛል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሀገራዊ ንቅናቄም ለአፍሪካ የአካባቢ ጥበቃ ጥረት አዲስ የተግባር ልምድ እየሆነ መጥቷል። የአረንጓዴ ዐሻራው ልዩነት በተተከሉ ችግኞች ቁጥር ብቻ አይለካም። በተራቆቱ መሬቶች ላይ የተመለሰው ሕይወት፣ በገጠር የተፈጠሩ የኢኮኖሚ ዕድሎች፣ የተጠበቁ የውሃ ሀብቶችና ለወደፊት ትውልድ የተገነባው የአካባቢ መሠረት ዋናው ውጤቱ ነው። አረንጓዴ ዐሻራ፤ ከርዕይ ወደ ተግባር!! የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በሀገራዊ ለውጥ ማግስት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በሕዝባዊ ተሳትፎ የተጀመረ ሲሆን፤ እስካሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ከዚህ በፊት የነበረው የተፈጥሮ ሃብት መራቆት በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ብቻ ሳይሆን በዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይም ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ ነበር። የአፈር መሸርሸር፣ የደን መጥፋትና የድርቅ ተጋላጭነቶችም የገጠር ሥነ-ምኅዳራዊ ሕይወትን ሲፈታተኑ ቆይተዋል። ይህን ምላሽ ለመስጠትም የአረንጓዴ ዐሻራ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማልማትና የደን ሽፋንን ከነበረበት 17 ነጥብ 2 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ በማሳደግ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። የአረንጓዴ አሻራ የኢኮኖሚ ዐሻራ፡- የአረንጓዴ ዐሻራ ትርጉም በአካባቢ ጥበቃ ብቻ አይወሰንም። በኢኮኖሚውም ውስጥ አዲስ የልማት መንገድ እየፈጠረ ይገኛል። በጥምር ግብርና (Agroforestry) አማካኝነት ቡና፣ ፍራፍሬና ሌሎች የኢኮኖሚ ዋጋ ያላቸው ምርቶች ከደን ልማት ጋር እንዲሰናሰሉ አድርጓል። ይህም የገቢ ምንጭን ከማስፋት ባሻገር የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ አስተዋፅዖ አድርጓል። በተለይ የቡና ዘርፍ ከሚሊዮን ወደ ቢሊዮን ዶላር ደረጃ መሻገሩ የዚህ ጥምረት ውጤት አንዱ ማሳያ ነው። የአቮካዶ ምርት ለወጪ ንግድ የፈጠረው ዕድልም አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ ውጤታማነት አብነት ሆኗል። በሌሎች የፍራፍሬ ምርቶች ላይ የመጣው ዕድገት ኢትዮጵያን በዓለም ገበያ የተሻለ ተወዳዳሪ የምትሆንበትን ዕድል ፈጥሯል። ከአፈር ጥበቃ እስከ ምግብ ዋስትና፡- የአረንጓዴ ዐሻራ በአፈር ጤናማነት ላይ ያመጣው ለውጥ የግብርና ምርታማነትን ከፍ አድርጓል። የአፈር ኦርጋኒክ ካርቦን መጨመር፣ የውሃ ማቆየት አቅም መሻሻልና የተፋሰስ ልማት በኢትዮጵያ የመስኖ ልማትና የምግብ ምርት ዕድገት መሠረት ጥለዋል። የስንዴ ምርታማነት ዕድገት እና የቤተሰብ ብልፅግናን የሚያረጋግጥ ስኬታማ ጉዞም የአረንጓዴ ዐሻራ ተጠቃሽ ውጤቶች ናቸው። የተፈጥሮ ጋሻነት፡- ኢትዮጵያ ለድርቅ፣ ለጎርፍና ለመሬት መንሸራተት ተጋላጭ ከሆኑ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ናት። ዛፎችና ስሮቻቸው አፈርን በመያዝ መሸርሸርን ይቀንሳሉ፤ የውሃ ሃብቶችን ጠብቆ በማቆየትና በማሻሻል የድርቅ ተጋላጭነትን የመቋቋም አቅም እየገነባ ነው። በተለይም በርካታ የኃይል ማመንጫ ግድቦችንና የውሃ ሃብቶችን ከደለል አደጋ ለመጠበቅ የደን ልማት ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ እሙን ነው። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም የተፈጥሮ አደጋዎችን በመቀልበስ የተፈጥሮ ጋሻነቱን እያረጋገጠ ይገኛል። የትውልድ ሐውልትና የልማት ውርስ የሆነው አረንጓዴ ዐሻራ!! የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የመንግሥትና የሕዝብ የጋራ ተሳትፎ ውጤት መሆኑን የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ በአንድ ወቅት ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻም፣ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው ዘመቻ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ተሳትፈውበታል። ይህም ኢትዮጵያዊያን የጋራ ታሪክ በመፃፍ በልማት መስክ አስደናቂ የትብብር መንፈስ እንዲገነቡ አስችሏል። የመርሃ ግብሩ ብሔራዊ የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አረንጓዴ ዐሻራ የደን ውድመትን በመከላከል የተፈጥሮ ሃብትን ለመጠበቅ፣ የድርቅና የበረሃማነት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እያስገኘ ነው። የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ተፅዕኖ መቋቋም አዲስ የዲፕሎማሲ ሚና!! በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረክ የአፍሪካ ዋና ጥያቄ የአየር ንብረት ፍትሐዊነት ነው። አህጉሪቱ በአነስተኛ የካርቦን ልቀት ላይ ብትገኝም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ከባድ ጫናን እየተጋፈጠች ይገኛል። በዚህ አውድ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራን እንደ ሀገራዊ ፕሮጀክት በመውሰድ ለአፍሪካ ሀገራት ጭምር የሚጋራ ተሞክሮ ፈጥራለች። የአፍሪካ አህጉራዊ የአየር ንብረት ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄዱም ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ ያላትን ተሳትፎና አመራር ያሳየ ክስተት ነው። ይህ ጉባኤ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የአየር ንብረት ውይይት ማዕከል እንድትሆን ከማገዙም በላይ የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮችን ለማስተናገድ ያላትን አቅም በተግባር አሳይቷል። ማጠቃለያ፡- የተተከለ ችግኝ፣ የተገነባ ተስፋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ ዳርቻ ''ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት፤ በዚህ ዓመት ስምንት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተቀምቷል። በዚሁ ወቅትም ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን ወደ 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በፅናት እየገሰገስን እንገኛለን ብለዋል፡፡ ዘንድሮም የተያዘውን የስምንት ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ስራ ላይ በሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ መትከል ብቻ አይደለም። የኢትዮጵያ የወደፊት የዕድገትና ብልፅግና ማሳኪያ የልማት ትልም እንጂ። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም ከአንድ ችግኝ ጀምሮ እስከ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረክ የደረሰ የሀገር ተሞክሮ ነው። የተተከሉት ችግኞች ዛሬ የአካባቢ ጥበቃ ዘብ ሲሆኑ፣ ነገ ደግሞ የኢኮኖሚ ዕድል፣ የምግብ ዋስትና፣ የኃይል ዘላቂነትና የትውልድ ተስፋ ይሆናሉ። የተተከለው ችግኝ ነገ የሚሆነው ዛፍ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬ፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ጋሻና ለመጪው ትውልድ የሚተላለፍ ሕያው ቅርስ ነው። አረንጓዴ ዐሻራ ዛሬ የሚተከል ተስፋ፣ ነገ የሚሰበሰብ ብልፅግና ነው፤ ተስፋን እንትከል!!!
የሌማት ትሩፋት፡ የኢትዮጵያ ግብርና በአዲስ ምዕራፍ
Jul 22, 2026 305
በሳባ ስለሺ መግቢያ ኢትዮጵያ ለዘመናት የነበራትን የግብርና እምቅ ሀብት ወደ ተጨባጭ የምግብ ዋስትና ለመቀየር ተግዳሮት ሆኖባት የቆየ ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግስት በተጀመረው ዘርፈ-ብዙ የሪፎርም ጉዞ የዘርፉ ታሪክ በተጨባጭ እየተቀየረ ነው። የዚህ ለውጥ አብይ ማሳያ የሆነውና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ ይፋ የሆነው "የሌማት ትሩፋት" መርሃ ግብር አንዱ ነው። ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ የሀገሪቱን የግብርና እና የእንስሳት ሀብት ልማት ጉዞ በአዲስ ምዕራፍ የቃኘ ነው። የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ሲሆን፣ በዋናነት በእንስሳት ሀብት እና ተያያዥ ዘርፎች ላይ ያተኩራል።በእንስሳት ሀብት ልማት ረገድ የወተት ላሞችን፣ የዶሮ (ሥጋ እና እንቁላል)፣ የንብ ማነብ (ማር) እና የዓሣ እርባታን በስፋት የሚያካትት ነው።የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ ኢትዮጵያን ከምግብ ሸማችነት ወደ አምራችነት በማሸጋገር የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ነው። በተለይም በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ፣ የኑሮ ውድነትን በማቃለል፣ የአርሶና አርብቶ አደሩን ገቢ በማሳደግ እንዲሁም ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት የምግብ ሉዓላዊነትን እውን ለማድረግ ያለመ ነው። የሌማት ትሩፋት ለምን አስፈለገ? ፡- የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር፣ ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የተፈጥሮ ሀብትና የሰው ኃይል በመጠቀም፣ ለዘመናት የዘለቀውን የምግብና ሥነ-ምግብ ዋስትና ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተነደፈ ነው። መንግስት ለዚህ መርሃ ግብር ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት የሚገኘውም፣ ሀገሪቱ ያላትን ከፍተኛ የእንስሳት ሀብት በቴክኖሎጂ በመደገፍ ወደ ተጨባጭ እሴትና የሀገር ውስጥ ተጠቃሚነት ለመቀየር እንዲሁም የዘርፉን ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ነው። ባለፉት አራት ዓመታት ምን ተከናወነ?፡- ባለፉት አራት ዓመታት በተተገበረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የወተት፣ የእንቁላል፣ የሥጋ፣ የዓሣ እና የማር ምርቶችን ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ ተከናውኗል። ለዚህ ስኬት በቂና ጥራት ያለው የእንስሳት ተዋጽኦ ለማቅረብ የሚያስችሉ ሰፊ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻልና የማዳቀል ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን፤ የአዳቃይ ቴክኒሻኖችን አቅም መገንባት፣ የፈሳሽ ናይትሮጂን አቅርቦትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለዘርፉ ተዋናዮች ማስተላለፍ ተችሏል። እንዲሁም የእንስሳት መኖ አቅርቦትንና ተደራሽነትን በማስፋፋት፣ የእንስሳት እርባታ ደህንነታቸውን በጠበቀ መልኩ እንዲከናወን በማድረግ እና አስፈላጊውን መሰረተ ልማት በማሟላት ረገድ ላለፉት አራት ዓመታት ቅድሚያ ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል። በመስኩ ምን ተጨባጭ ውጤት ተገኘ ?፡- የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የሀገሪቱን የምግብና ስነ-ምግብ ደህንነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በዜጎች ዘንድ የቆየውን አመለካከት በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ለውጥ አስመዝግቧል። በተለይም በገጠሪቱ የሀገሪቱ ክፍል ብቻ ተወስኖ የነበረውን የግብርና እንቅስቃሴ ወደ ከተሞች በማስፋት፣ ህጻናት፣ እናቶች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ከእንስሳት ተዋጽኦ ማግኘት የሚገባቸውን አስፈላጊ ንጥረ ነገሮች እንዲያገኙ አስችሏል። ይህ ተነሳሽነት የከተማ ግብርናን በማስተዋወቅ ዜጎች በቤታቸው እንስሳትን በማርባት ከራስ ፍጆታ ባለፈ ምርቶቻቸውን ለገበያ በማቅረብ የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል። በመሆኑም፣ ባለፉት ዓመታት በመስኩ የተመዘገቡት ስኬቶች እንደሚያሳዩት፣ መርሃ ግብሩ ዜጎች በተቋማት ተቀጥረው ከመስራት ይልቅ በዘርፉ ተሰማርተው የራሳቸው ስራ ኖሯቸው ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ አድርጓል። ይህ የመንግስት ያላሰለሰ ጥረት፣ የዜጎችን የስነ-ምግብ ፍላጎት ከማሟላት አልፎ፣ ጤናማ እና ሁለንተናዊ ብቃት ያለው ትውልድ በመገንባት ሂደት ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በአሀዛዊ መረጃ የተደገፉ የዘርፉ ስኬቶች ፡- የግብርና ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው አኃዛዊ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በተጀመረ በአራት ዓመታት (2014 ዓ.ም -2018 ዓ.ም) ውስጥ በእንስሳት ምርታማነት አስደናቂ ለውጥ ተመዝግቧል። በወተት ምርት፦ መርሃ ግብሩ ሲጀመር የነበረው 7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ሊትር የማምረት አቅም፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 15 ነጥብ 7 ቢሊዮን ሊትር አድጓል። በእንቁላል ምርት፦ ከነበረበት 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን በከፍተኛ ሁኔታ በማደግ፣ ወደ 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን ከፍ ብሏል። በዶሮ ሥጋ ምርት፦ በ2014 ዓ.ም 90 ሺህ ቶን የነበረው የማምረት አቅም፣ በ2018 ዓ.ም ወደ 253 ሺህ ቶን ከፍ ብሏል። በማር ምርት፦ በ2014 ዓ.ም 146 ነጥብ 7 ሺህ ቶን የነበረው የማምረት አቅም፣ በ2018 ዓ.ም ወደ 428 ሺህ ቶን ከፍ ብሏል። በአሳ ምርት፦ የውሃ አካላትንና ሰው ሰራሽ ኩሬዎችን በአግባቡ በመጠቀም የተከናወነው የአሳ ጫጩት ስርጭት፣ ከ300 ሺህ ወደ 16 ነጥብ 5 ሚሊዮን አድጓል። ይህ ውጤት ሀገሪቱ በእንስሳት ተዋጽኦ ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም በጥቂት ዓመታት ውስጥ እንዴት ማጎልበት እንደተቻለ በግልጽ ያሳያል። ዘርፉ ለውጭ ምንዛሪ ግኝት ምን አበረከተ?፡- የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የሀገር ውስጥ የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢትዮጵያ ከእንስሳት ተዋፅኦ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ አስቻይ ሁኔታዎችን ፈጥሯል። በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ብቻ 24 ነጥብ 2 ሺህ ቶን የተቀነባበረ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን ለዓለም አቀፍ ገበያ በማቅረብ 128 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል። ማጠቃለያ፦ በዘርፉ የተመዘገበውን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ አርብቶ አደር እና አርሶ አደሩ ከተለመደው ባህላዊ የእንስሳት አረባብ ዘዴ ለማላቀቅ የተጀመሩ ስራዎችን ማስቀጠል፣ የእንስሳት መኖ አቅርቦትንና ጤና አገልግሎትን የማዘመን፣ እንዲሁም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅና የማምረት አቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው። በተጨማሪም የመንግስት፣ የግሉ ዘርፍ እና የማህበረሰቡን ቅንጅት ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አሰራር መዘርጋት፣ የቴክኖሎጂ ድጋፍ ያለው የገበያ ትስስር መፍጠርና የደላሎችን ጣልቃ ገብነት ማስወገድ እንዲሁም አምራቹና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ለተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ጠንካራ መሰረት ማኖር ይቻላል። በአጠቃላይ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የግብርና እምቅ ሀብት ወደ ተጨባጭ ሀገራዊ ብልፅግና ለመቀየር የተጀመረ ውጤታማ መንገድ መሆኑን ባለፉት አራት ዓመታት አሳይቷል። ይህ ከተጠናከረ ሀገሪቱ የምግብ ሉአላዊነቷን ለማረጋገጥ ያለመችውን ትልም ከማሳካት የሚያስቆማት ነገር እንደማይኖር አመላካች ነው።
ሀገራዊ ምክክር፡ለተሻለች ኢትዮጵያ የተከፈተ በር
Jul 22, 2026 197
በኢትዮጵያ ለዓመታት የቆዩ አለመግባባቶችና ችግሮች ብዙ ናቸው።እነዚህ አለመግባባቶች የሀገር ሰላም፤አንድነት፤ልማት እድገትና የዜጎችን የወደፊት ተስፋ የሚፈታተኑ ሆነው ቆይተዋል። አለመግባባቶችን በኃይል ለመፍታት የተደረጉ ሙከራዎች ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጡ አልቻሉም። ስለዚህ የጥላቻን፣የበቀልንና የመከፋፈልን ዑደት ለማቆም የሚያስችል ትክክለኛ መንገድ ውይይት፣መደማመጥና መግባባት መሆኑ በስፋት እየታመነ መጥቷል። በዚህ መነሻ፣ኢትዮጵያ በታሪኳ ታላቅ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እያካሄደች ትገኛለች።ይህ ምክክር ዜጎች ሀሳባቸውን በነፃነት የሚገልጹበትና የጋራ መፍትሄ የሚፈልጉበት መድረክ ሆኗል። የሀገራዊ ምክክሩ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር ሳይሆን፣ የሁሉንም ወገን ድምጽ በማዳመጥ የጋራ መግባባት መፍጠር ነው። ይህ ምክክር በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተወከሉ ዜጎች ድምጽ የሚሰማበት፣አመለካከቶች የሚተነተኑበትና የጋራ መፍትሄዎች የሚፈለጉበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሆኗል። ሀገራዊ ምክክሩ የተለያዩ ወገኖችን በአንድነት በማሰባሰብ፣የከረሙ ችግሮችን በተቀናጀ መንገድ በመፍታት፣ የፖለቲካዊ፣የኢኮኖሚያዊና የማህበራዊ ለውጦችን ለማምጣት ይረዳል። እንዲሁም ኢትዮጵያን ወደ አንድነት፣ሰላምና ብልጽግና ለማሸጋገር የሚያገለግል ታላቅ መድረክ ነው። ሀገራዊ ምክክር ማድረግ ብቸኛው መንገድ ነው ብለው ያመኑ ኢትዮጵያዊያንም ከሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫ እና ከውጭ ጭምር በመምጣት በአዲስ አበባ ተገናኝተው ስለሀገራቸው እየመከሩ ይገኛል። በሁሉም ክልሎች፣በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮችና በውጭ ከሚኖሩ ዜጎች ሕዝብ የወከላቸው ተመካካሪዎችም በንዑስ ቡድኖች በመከፋፈል በተመደቡበት አጀንዳ ላይ መመካከር መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል። በሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ሂደት ጠንካራ መግባባትን የሚፈጥር ግልፅና ተስፋ ሰጪ ምክክር እያደረግን ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተመካካሪዎች በበኩላቸው ገልጸዋል። የሀገራዊ ምክክሩ ስኬት የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን ከመላው ኢትዮጵያዊያን ተሳትፎ ጋር የሚያያዝ ነው። ዛሬ በምክክር የምንገነባው መግባባት፣ነገ ለመጪው ትውልድ የተረጋጋች፣የተባበረች፣ሰላማዊና የበለፀገች ኢትዮጵያን የሚያስረክብ መሠረት ይሆናል። ይህ ሀገራዊ ምክክር የጋራ መግባባት ባህልን ለማጠናከር፤ለፀናችና ለተሻለች ኢትዮጵያ የተከፈተ ትልቅ በር ነው።
የኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነት፤ ራስን ለመቻል የተደረገ ሽግግር
Jul 21, 2026 483
በ አሸናፊ በድዬ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት፣ የብዙኃኑ ዜጋ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆነ የሥራ ዕድል መፍጠሪያ፣ እንዲሁም ለአጠቃላይ ሀገራዊ ዕድገት (ጂዲፒ) ከ33 በመቶ በላይ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሠረታዊ ዘርፍ ነው። ይሁን እንጂ ላለፉት አሥርት ዓመታት የሀገሪቱ ግብርና በዝናብ ጥገኝነት፣ በባህላዊና ኋላ ቀር የሞፈርና ቀንበር የአመራረት ዘይቤ፣ በአፈር መሸርሸር እንዲሁም በዝቅተኛ ምርታማነት ምክንያት የወቅቱን የሕዝብ ቁጥር ዕድገት መመጠንና የዜጎችን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ተስኗት ቆይቷል። ሀገሪቱ በየዓመቱ ለረድኤት እና ለውጭ እርዳታ እጇን እንድትዘረጋ፣ እንዲሁም ለዕለት ጉርስ የሚሆን እህል ከውጭ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንድታስገባ ተገዳ ነበር። ይሁን እንጂ፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት የተጀመሩ ፕሮጀክቶች፣ በእርሳቸው የቅርብ አመራር ሰጪነት የተጀመሩት አዳዲስ ፖሊሲዎችና መዋቅራዊ ማሻሻያዎች ዘርፉን ሙሉ በሙሉ እየቀየሩት ይገኛሉ። ይህ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ የሀገሪቱን ግብርና ከባህላዊና ለዕለት ፍጆታ ብቻ ከሚመረተው የህልውና ግብርና ወደ ዘመናዊ፣ በቴክኖሎጂ ወደታገዘና ከፍተኛ ትርፍ ወደ የሚያስገኝ የንግድ ግብርና እያሸጋገረው ይገኛል። በኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የተመዘገቡ ታሪካዊ ስኬቶችን፣ የምግብ ዋስትናን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት የተወሰዱ ቁልፍ እርምጃዎችን እና የዘርፉን የወደፊት ብሩህ ተስፋዎች እንመልከት፦ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ስኬት ኢትዮጵያ ከሀገራዊ ለውጡ በፊት በየዓመቱ ለስንዴ ፍጆታ ማሟያ የሚሆን እስከ አንድ ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የውጭ ምንዛሬ ታወጣ ነበር። ይህን ከፍተኛ ወጪ ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት እና የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የቆረጠችበት ትልቁና ህያው ማሳያ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ፕሮጀክት ነው። ይህ ተግባር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ልዩ ክትትል፣ የመስክ ምልከታና አነሳሽነት የተጀመረ ሲሆን፣ በአጭር ዓመታት ውስጥ በሀገሪቱ የግብርና ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ተጨባጭ ተአምር ያሳየ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ሆኗል። ሀ. የአመራረት ስር ነቀል ለውጥ ቀደም ሲል ስንዴ በኢትዮጵያ ይመረታል ተብሎ የሚታሰበው በክረምት ዝናብ ብቻ እና በደጋማ አካባቢዎች ነበር። ይህንን የተለመደ አሠራር በመለወጥ፣ በበጋ ወቅት ምንም ዝናብ በሌለበት ያሉትን ወንዞች፣ የውሃ አማራጮችን እና የከርሰ-ምድር ውሃን በመጠቀም በመስኖ የማልማት ሥራ በስፋት ተተገበረ። ይህም አርሶ አደሩ በአንድ መሬት ላይ በዓመት ሁለት እና ሦስት ጊዜ ሰብል እንዲያመርት በማስቻል የምርት ወቅትን በእጥፍ አሳድጎታል። ባህላዊውን ዝናብ ጠባቂነት ወደ ቴክኖሎጂና ውሃ መሪ ግብርና የለወጠ ታሪካዊ ሽግግር ነው። ለ. የመሬት ስፋትና የምርት ዕድገት ፕሮጀክቱ በ2012 ዓ.ም. አካባቢ በጥቂት ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በሙከራ ደረጃ የተጀመረ ቢሆንም፤ በአሁኑ ወቅት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሄክታር መሬቶችን ማሸፈን ችሏል። የመሬት ስፋት አድማስ፦ መጀመሪያ ላይ በደጋማ ቦታዎች ብቻ የነበረው ስንዴ፣ አሁን ላይ ሰፊና ምቹ ሜዳዎች ወደሚገኙባቸው ዝቅተኛና ሞቃታማ የቆላ አካባቢዎች (Lowlands) እንዲስፋፋ ተደርጓል። የምርታማነት መጨመር፦ በኩታ ገጠም (Cluster) እርሻ አሠራር፣ በምርጥ ዘር አቅርቦት እና በሜካናይዜሽን (በትራክተርና ኮምባይነር) አጠቃቀም ምክንያት በሄክታር የሚገኘው የምርት መጠን በአማካይ ከ35 እስከ 45 ኩንታል እና ከዚያ በላይ አድጓል። ይህም በአጠቃላይ ሀገራዊ የስንዴ ምርትን በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኩንታሎች እንዲጨምር አድርጓል። ሐ. ከገቢ ምርት ወደ ውጭ ንግድ፡- ይህ ስልታዊ ስኬት ኢትዮጵያን ለዓመታት ተጭኗት ከነበረው የስንዴ ተረጂነትና ከውጭ የማስገባት ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በኩራት ያላቀቃት ታላቅ ድል ነው። ራስን መቻል፦ ሀገሪቱ በውስጥ ምርቷ ፍላጎቷን ማሟላት መቻሏ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈጠሩ የጂኦፖለቲካ ቀውሶች (ለምሳሌ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ያስከተለው የስንዴ እጥረት) በኢትዮጵያ ላይ የከፋ የምግብ እጥረት እንዳያመጡ ትልቅ ጋሻ ሆኗል። ወደ ውጭ መላክ፦ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ የተረፈውን ምርት ለጎረቤት ምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት እንዲሁም ለዓለም አቀፍ ገበያ በይፋ መላክ የተጀመረበት ታሪካዊ ምዕራፍ ተመዝግቧል። ይህ ስኬት ሀገሪቱ የምግብ ዋስትናዋን በራሷ አቅም ከመገንባቷም በላይ፣ ግብርናን አዲስ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ የኢኮኖሚ ምንጭ እንዲሆን አድርጎታል። የሌማት ትሩፋት" ንቅናቄና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ማለት የዜጎችን ሆድ በካሎሪ (በእህል ምርት) መሙላት ብቻ ሳይሆን፣ የአዕምሮና የአካል እድገትን የሚወስነውን የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ ማለት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በይፋ ያስጀመሩት የሌማት ትሩፋት ሀገራዊ ንቅናቄ ዋና ስትራቴጂካዊ ግብም ይሄው ነው፦ በሀገሪቱ የተመጣጠነ ምግብ በየቤተሰቡ ደረጃ ማሳደግ የታለመለት ግብ ነው።ይህ ንቅናቄ በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ ተገንብቶ ከፍተኛ ስኬት አስመዝግቧል። የእንስሳት ሀብትና የወተት ልማት፦ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀዳሚውን የእንስሳት ሀብት የያዘች ቢሆንም፣ ቀደም ሲል የሚገኘው የወተት ምርት እጅግ ዝቅተኛ ነበር። አራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን የወተት ላሞችን ለማዳቀል የተያዘው እቅድ እየተሳካ ይገኛል። በንቅናቄው ከፍተኛ የወተት ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ በማቅረብ፣ ዘመናዊ የእንስሳት መኖ አጠቃቀምን በማስፋፋት እና በኩታ ገጠም አሠራር የወተት ማቀነባበሪያዎችን በመገንባት የወተት ምርት በዓመት ከሰባት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ወደ 16 ቢሊዮን ሊትር ማሳደግ አስችሏል። የዶሮና የእንቁላል ምርት ማዕበል፦ በዝቅተኛ ቦታና ወጪ ፈጣን የፕሮቲን ምንጭ ለማግኘት የዶሮ እርባታን ማዘመን ቁልፍ እርምጃ ነበር። በሚሊዮን የሚቆጠሩ የ45 ቀናት የውጭ ድቅል ጫጩቶች ለገጠርና ለከተማ ነዋሪዎች ተሰራጭተዋል። ይህ አሠራር ቀደም ሲል በዓመት ጥቂት እንቁላል ብቻ ከምትጥለው የሀገር ውስጥ ዶሮ ተሻሽሎ፣ በቀጣይነት ለገበያና ለቤት ውስጥ ፍጆታ የሚውል የእንቁላልና የሥጋ ምርትን አሳድጓል። ባለፉት ዓመታት 160 ሚሊዮን ጫጩቶችን ለማሰራጨትና 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን እንቁላል ለማምረት የተያዘው ግብም በውጤታማነት እየተጓዘ ይገኛል። የንብ ማነብ (የማር ልማት)፦ ኢትዮጵያ ያላትን የበለጸገ የተፈጥሮ ዕፅዋት እምቅ አቅም በመጠቀም ባህላዊ ቀፎዎችን በዘመናዊ ቀፎዎች የመተካት ሥራ በስፋት ተከናውኗል። ይህም በአንድ ቀፎ የሚገኘውን የማር ምርት ከ7 ኪሎ ግራም ወደ 20-30 ኪሎ ግራም በማሳደግ አርሶ አደሩን ተጨማሪ የገቢ ባለቤት አድርጎታል። ለዚህም የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ጉልህ ሚና በማበርከት ላይ ይገኛል። የአሳ ሀብት ልማት፦ በተፈጥሮ ሐይቆች ላይ ብቻ የነበረውን ጥገኝነት በመስበር፣ በየገጠሩ ሰው ሠራሽ የውሃ ማቆሪያዎችና ኩሬዎችን በመጠቀም የዓሣ እርባታ ተጀምሯል። ይህ ሥራ በተለይ የወንዝ ተፋሰስ ባላቸው አካባቢዎች ማኅበረሰቡ የዓሣ ምርትን በምግብ ሰንሰለቱ ውስጥ እንዲያካትት አግዟል። የብዙኃኑ ተስፋዎች በኢትዮጵያ ግብርና ላይ የመጣው ለውጥ ወቅታዊ ስኬት ብቻ ሳይሆን የወደፊቷን ጠንካራ ሀገር የመገንባት መዋቅራዊ መሠረት ነው። ሀገሪቱ ለዘመናት ከነበረችበት የድርቅና የእርዳታ እህል ጠባቂነት ታሪክ ወጥታ፣ ስንዴን ወደ ውጭ የምትልክ፣ በሌማት ትሩፋት የተመጣጠነ ምግብን የምታረጋግጥ እና አረንጓዴ ዐሻራን በመጠቀም የአየር ንብረቷን የምትጠብቅ ታላቅ ሀገር መሆን እንደምትችል በተግባር አሳይታለች። እነዚህ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሲቀጥሉ፣ የኢትዮጵያ ግብርና የሀገር ውስጥ ፍላጎትን በራስ አቅም ከማሟላት አልፎ የምሥራቅ አፍሪካና የመላው አህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ማዕከል (Breadbasket of Africa) የመሆን ዕቅዷን ሙሉ በሙሉ እውን እንደሚያደርገው ምንም ጥርጥር የለውም።
ትንታኔዎች
የኢትዮጵያዊያን ምክክር፤ የጋራ ነገን የሚያሻግር የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ድልድይ
Jul 22, 2026 302
በሚኪያስ ጎቡ መግቢያ፡- ሀገራት ከጦርነት በላይ የሚፈትናቸው ጠላት አለ፤ እርሱም በአንድ ሀገር ልጆች መካከል የሚፈጠረው የመተማመን መሰናክል ነው። መሣሪያ የፈጠረውን ጉዳት እንደገና መገንባት ይቻላል። የተሰበረ ልብና የጠፋ መተማመን ግን በጉልበት አይመለስም። ለዚህም ነው ብዙ ሀገራት ከግጭት በኋላ ወደ ምክክር የሚመለሱት። ብሔራዊ ምክክር የአንድ መንግሥት ፕሮጀክት ወይም የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአንድ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፈው የሰላም ውርስ ነው። የሚጋጩ ሃሳቦች በጠመንጃ ሳይሆን በቃል ሲገናኙ፣ የተለያዩ ትርክቶች በመደማመጥ ሲቀራረቡ፣ ልዩነቶችም የጥላቻ ምንጭ ሳይሆኑ የመግባባት መነሻ ሲሆኑ ነው እውነተኛ ሀገራዊ ምክክር የሚፈጸመው። የዓለም ተሞክሮ እንደሚያሳየው ብሔራዊ ምክክር አንድ ዓይነት ቀመር የለውም። እያንዳንዱ ሀገር በታሪኩ፣ በባህሉ፣ በፖለቲካዊ እውነታውና በማኅበራዊ መዋቅሩ መሰረት የራሱን መንገድ ይመርጣል። ነገር ግን የሁሉም ግብ አንድ ነው፤ ግጭትን በመግባባት፣ ጥላቻን በመተማመን፣ ፍርሃትን በተስፋ መተካት። በአውሮፓ ከኮሙኒዝም ውድቀት በኋላ፣ በአፍሪካ ከአምባገነናዊ አስተዳደሮች ሽግግር ወቅት፣ በደቡብ አሜሪካ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሂደቶችና በዓረቡ ዓለም ከፖለቲካ አብዮቶች በኋላ የተካሄዱ ምክክሮች አንድ ትልቅ ትምህርት ይሰጣሉ። ምክክር ሲታመን ሀገር ያድናል፤ ለፖለቲካ ጥቅም ሲውል ግን ቀውስን ያባብሳል። ይህ የኢትዮጵያም ትልቁ ፈተና ነው። ሀገራዊ ምክክር የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ወገን ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነት ነው። የምንናገረው ቃል፣ የምንጽፈው ሐሳብ፣ የምናዳምጠው አቋምና የምንቀበለው ልዩነት የነገዋን ኢትዮጵያ ይቀርጻሉ። ምክክር የሚጀምረው በአዳራሽ ሳይሆን በሰዎች ልብ ውስጥ ነው፤ የሚሳካውም ከመናገር በላይ በመደማመጥ ሲቻል ነው። ስለዚህ የዛሬው ጥያቄ "ምክክር ይካሄድ ወይ?" የሚል አይደለም። "ምክክሩን ለሀገር የሚበጅ፣ ለትውልድ የሚተርፍ፣ ለታሪክ የሚያስከብር እንዴት እናድርገው?" የሚለው ነው። መልሱም በአካታችነት፣ በእውነት፣ በመከባበርና በሀገርን ከግል ጥቅም በላይ በማስቀደም ውስጥ ይገኛል። ምክክር፤ የሀገር መድኃኒት ወይስ የትውልድ ፈተና? ምክክር ለምን ያስፈልጋል?፡- ማንኛውም ሀገር የሚያድገው በሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ግንባታ ብቻ አይደለም። በሕዝቦቿ መካከል በሚኖረው መተማመን ጭምር እንጂ። መንገድ፣ ድልድይና ፋብሪካ መገንባት ይቻላል፤ ነገር ግን የተሰበረ ማኅበራዊ ትስስር ካልተጠገነ የልማቱ መሠረት ይናወጣል። ስለዚህ ብሔራዊ ምክክር የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን የሀገር የወደፊት ዕጣ ፋንታ የሚወሰንበት የጋራ አስተሳሰብ ሂደት ነው። የምክክሩ ዋና ዓላማ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር አይደለም። ይልቁንም ሁሉም ወገኖች የራሳቸውን እውነት እየገለጹ፣ የሌላውንም እውነት በማዳመጥ የጋራ መግባባት የሚፈጥሩበት ሂደት ነው። እውነተኛ የምክክር ድል የሚለካውም የማን ሃሳብ አሸነፈ ሳይሆን ለሀገር ምን ያህል ሰላምና መተማመን ፈጠረ በሚለው ነው። የዓለም ተሞክሮ የሚያስተምረን፡- የታሪክ ገጾች እንደሚያሳዩት ሀገራት የብሔራዊ ምክክርን መንገድ የመረጡት ሌሎች አማራጮች ሲያቅቷቸው ነው። አንዳንዶቹ የረዥም ጊዜ የፖለቲካ ቀውስ ነበራቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ በዘር፣ በሃይማኖት ወይም በሥልጣን ሽኩቻ ተከፋፍለው ሲራኮቶ የሰነባበቱ ናቸው። ነገር ግን የተሳካላቸው ሀገራት አንድ የጋራ መርህ ነበራቸው፤ የሀገርን ጥቅም ከፓርቲ፣ ከቡድንና ከግል ጥቅም በላይ አስቀድመዋል። ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ ወደ ዴሞክራሲ የተሸጋገረችው በበቀል ሳይሆን በሰለጠነ ምክክር ነው። ፖላንድና ሀንጋሪ የፖለቲካ ሽግግራቸውን በየጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር አሳልፈዋል። ላይቤሪያና ሊባኖስ የጦርነት ቁስላቸውን ለማዳን የመደማመጥን መንገድ መርጠዋል። በተቃራኒው ግን ምክክርን ለፖለቲካ ሕጋዊነት ማግኛ፣ ለሥልጣን ማራዘሚያ ወይም ለውጭ ጫና ማስታገሻ ብቻ ያደረጉ ሀገራት የበለጠ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። ይህም አንድ ግልጽ ትምህርት ይሰጠናል፤ የምክክር ስኬት የሚወሰነው በመድረኩ ሳይሆን በተመካካሪዎች ቅንነት መሆኑን ያስረዳናል። ምክክር የሚጠይቀው ከባድ ኃላፊነት፡- ሀገራዊ ምክክር የኮሚሽን ወይም የመንግሥት ሥራ ብቻ አይደለም። የሁሉም ዜጎች የጋራ ኃላፊነትን የሚጠይቅ የጋራ ነገ አሻጋሪ ድልድይና የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ ነው። ፖለቲከኛው የሀገርን ጥቅም ማስቀደም፣ የሚዲያው እውነትን በሚዛናዊነት ማቅረብ፣ የሲቪክ ማኅበራት የተገለሉ ድምፆችን ማሰማት፣ የኃይማኖት ተቋማት ይቅርታና መቻቻልን ማስፋፋት፣ ወጣቱ ከጥላቻ ይልቅ ውይይትን መምረጥና ምሁራን በማስረጃ የተደገፈ ሃሳብ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ማንም ወገን የራሱን አቋም ብቻ ለማስገደድ ከሞከረ፣ ምክክሩ ወደ ክርክር ይቀየራል። ሁሉም ለመረዳት እንጂ ለማሸነፍ ካልመጡ ደግሞ የምክክሩ መንፈስ ይጠፋል። የሀገራዊ ምክክር ትልቁ ድል የሌላውን አቋም መለወጥ ሳይሆን፣ የሌላውን ህመም መረዳት ነው። ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር፤ ልዩነታቸው ምንድን ነው?፡- ብዙ ጊዜ ምክክር፣ ውይይት፣ ድርድርና ክርክር የሚሉት ቃላት በአንድ ትርጉም ይጠቀሳሉ። ነገር ግን በፖለቲካዊና በማኅበራዊ ሂደቶች እያንዳንዳቸው የተለየ ዓላማና ባህሪ አላቸው። ይህንን ልዩነት አለማወቅ ሀገራዊ ምክክርን ከመጀመሪያው ሊያዛባው ይችላል። ውይይት የሐሳብ ልውውጥ ነው። ሰዎች ስለ አንድ ጉዳይ አመለካከታቸውን ይገልጻሉ፣ ይደማመጣሉ። ሁልጊዜ ውሳኔ ላይ ላይደርስ ይችላል። ክርክር የሚያተኩረው የማን ሃሳብ ትክክል እንደሆነ ላይ ነው። የራስን አቋም በማስረጃ ለማስረዳት ይደረጋል፤ አንድ አሸናፊና አንድ ተሸናፊ ሊኖር ይችላል። ድርድር ደግሞ የጥቅም ግጭትን በመካከለኛ መፍትሔ ለመፍታት የሚደረግ ሂደት ነው። እያንዳንዱ ወገን ከአቋሙ በመቀነስ የጋራ መፍትሔ ለማግኘት ይሞክራል። ሀገራዊ ምክክር ግን ከእነዚህ ሁሉ የላቀ ሂደት ነው። ዓላማው ማንንም ማሸነፍ ወይም ማስሸነፍ ሳይሆን የሀገር የወደፊት አቅጣጫ ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር ነው። በምክክር ውስጥ የሚሸነፍ ሰው የለም፤ የሚያሸንፈው ሀገር ነው። የኢትዮጵያ ልዩ እውነታ፡- ኢትዮጵያ ሦስት ሺህ ዘመናትን የተሻገረ በሕብር ያሸበረቀ ታሪክ፣ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ፣ ቋንቋ፣ ባህልና ኃይማኖት ያላት ሀገር ናት። ይህ በሕብር ያሸበረቀ ልዩነት የኢትዮጵያ ጥንካሬ መሆን ሲገባው በተለያዩ ወቅቶች የፖለቲካ አለመግባባቶችና የታሪክ ትርክቶች የመከፋፈል መሣሪያ ሆነው ቆይተዋል። የሀገራዊ ምክክሩ ዋና ፈተናም ይህ ነው። ሁሉም የራሳቸውን ታሪክ ይዘው ወደ ጠረጴዛው ይመጣሉ፤ ነገር ግን ከጠረጴዛው የሚወጡት አንድ የጋራ የወደፊት ርዕይ ይዘው መሆን አለባቸው። ይህ ቀላል አይደለም። ስለዚህ ምክክሩ ከቃላት በላይ በተግባር የሚገለጥ ቅንነትን ይፈልጋል። የዋናው ምክክር ጉባኤ የህዝብ ወኪል ተመካካሪዎችም ሀገርን የማስቀደም ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ስኬታማ ምክክር የሚመሰረትባቸው አምስት ምሰሶዎች፡- ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ እንዲሆን ቢያንስ አምስት መሠረታዊ ምሰሶዎች ሊኖሩት ይገባል። እነሱም መተማመን፣ አካታችነት፣ እውነት፣ ፍትሕና የጋራ ርዕይ ናቸው። ከሁሉም ክልሎች፣ ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እና በውጭ ከሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበራሰብ የሕዝብ ወኪል 4 ሺ ተመካካሪ ኢትዮጵያዊያንም በሀገር ግንባታ ጉዳይ፣ የመንግስት አደረጃጃትና ስርአት ጉዳይ፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬድዋ ከተሞች ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና የመልካም አስተዳዳር ጉዳዮች፣ የሰላም ግንባታ ጉዳዮች በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽ ማዕከል እየመከሩ ይገኛል። ሀገራዊ ምክክር ያለፈውን ለመቁጠር ሳይሆን፣ የወደፊቱን ለመገንባት የሚደረግ የጋራ ጉዞ ነው። የኢትዮጵያ መንገድም የልዩነት ግድግዳን የሚያፈርስ የትውልድ አደራና የብሔራዊ መግባባት ማሰሪያ ጥበብና ትልም ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፤ የተገኙ ዕድሎች፣ ዋና ፈተናዎች እና የወደፊት አቅጣጫ በታሪክ ጉዞዋ ውስጥ ኢትዮጵያ ብዙ የፈተና ዘመናትን አልፋለች። አንዳንዶቹ ፈተናዎች ከውጭ ጥቃት የመጡ ቢሆኑም፣ አብዛኞቹ ግን ከውስጣዊ አለመግባባቶች፣ ከተለያዩ የታሪክ ትርክቶች፣ ከፖለቲካ ፉክክርና ከመተማመን እጥረት የተፈጠሩ ናቸው። ስለዚህ የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደት የዛሬን ችግር ለመፍታት ብቻ ሳይሆን፣ የትውልድ ዕዳን ለማቃለል የተጀመረ ታሪካዊ ሂደት ነው። ይህ ሂደት ቀላል አይደለም። በርካታ ዓመታት የተከማቹ ቅሬታዎች፣ የተለያዩ እውነታዎች፣ የተቃራኒ ትርክቶችና የተለያዩ የፖለቲካ ፍላጎቶች በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መገናኘታቸው በራሱ ትልቅ ፈተና ነው። ነገር ግን ከዚህ በላይ ትልቁ ፈተና ልዩነትን ወደ መግባባት መቀየር ነው። ዕድሎች፤ ሊጠቀሙባቸው የሚገቡ ወሳኝ መስኮቶች፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት ኢትዮጵያ ለብዙ ዓመታት ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ የምታነሳበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። የታሪክ አተረጓጎም፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የሥልጣን ክፍፍል፣ የሀብት አጠቃቀም፣ የፍትሕ ጉዳዮችና የአብሮነት ዕሴቶች በጦርነት ሳይሆን በሐሳብ የሚፈቱበት ዕድል ይፈጥራል። ከዚህም በላይ ምክክሩ የፖለቲካ ባህልን ለመቀየር የሚያስችል ዕድል ነው። ለብዙ ዓመታት "አሸናፊና ተሸናፊ" በሚለው አስተሳሰብ የተመራውን ፖለቲካ ወደ "አብሮ ማሸነፍ" የሚሸጋግር ከሆነ እውነትም የኢትጵያ የዴሞክራሲ ጉዞ ጠንካራ መሠረት ያገኛል። በሂደቱ ፊት የሚቆሙ ፈተናዎች፡- ማንኛውም ሀገራዊ ምክክር ከፍተኛ ተስፋ እንደሚፈጥር ሁሉ ከባድ ፈተናዎችንም ይዞ ይመጣል። የመጀመሪያው ፈተና የመተማመን እጥረት ነው። ለብዙ ዓመታት የተገነባ ጥርጣሬ በጥቂት ወራት አይጠፋም። ስለዚህ የምክክሩ ተዓማኒነት በእያንዳንዱ እርምጃ ሊገነባ ይገባል። ሁለተኛው ፈተና የተለያዩ የታሪክ ትርክቶች ናቸው። አንድ ክስተት በአንዱ ወገን የድል ታሪክ ሲሆን፣ በሌላው ወገን የመከራ ታሪክ ሊሆን ይችላል። ይህን ልዩነት በክብር መቀበል እንጂ መግፋት አይቻልም። በሌላ መልኩም የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ ስርጭት ነው። በዲጂታል ዘመን አንድ ያልተረጋገጠ መረጃ በጥቂት ደቂቃዎች ሺዎችን ሊደርስ ይችላል። ስለዚህ የሚዲያ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሚወስዱት ኃላፊነት ከመቼውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። የምሁራንና የመገናኛ ብዙኅን ሚና፡- በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ምሁራን ስሜትን ሳይሆን ማስረጃን ማቅረብ አለባቸው። የማኅበረሰብ ችግሮችን በሳይንሳዊ ጥናት መተንተን፣ ከሌሎች ሀገራት ልምድ መማርና አማራጭ መፍትሔዎችን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። መገናኛ ብዙኅንም በዚህ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና አላቸው። መገናኛ ብዙኅን ወሬን ከማባዛት ይልቅ እውነትን ማጣራት፣ ልዩነትን ከማባባስ ይልቅ መግባባትን ማጎልበት፣ ስሜትን ከማቀጣጠል ይልቅ እውነታን ማቅረብ አለበት። ምክክሩን የሚያጠናክር የመገናኛ አውታር ታሪክ ይሠራል፤ የሚያደናቅፍ ደግሞ በታሪክ ይጠየቃል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ቀን የሚጠናቀቅ ክስተት አይደለም። ምክክር በትውልድ የሚገነባ የፖለቲካ ባህል ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራውን ሊጨርስ ይችላል፤ ነገር ግን የመደማመጥ ባህል በሕዝብ ውስጥ ካልሰረጸ የምክክሩ እውነተኛ ዓላማ አይሳካም። የዛሬ ውሳኔ፤ የነገ ኢትዮጵያ፡- አንዳንድ የታሪክ ወቅቶች በየቀኑ አይመጡም። አንዳንድ ውሳኔዎችም የአንድ መንግሥት ዘመንን ብቻ ሳይሆን የትውልዶችን ዕጣ ፈንታ ይወስናሉ። ሀገራዊ ምክክር የእነዚህ ታሪካዊ ውሳኔዎች አንዱ ነው። ዛሬ በምንመርጠው የምክክር ባህል፣ በምንገነባው መተማመንና በምናሳየው የፖለቲካ ብስለት ላይ የነገዋን የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ተምሳሌት ኢትዮጵያ ያንፃል። ምክክር ሁሉንም ችግር በአንድ ጊዜ የሚፈታ አስማታዊ መፍትሔ አይደለም። ነገር ግን ጦርነትን ከውይይት፣ ጥላቻን ከመቻቻል፣ መከፋፈልን ከመተባበር የሚተካ ብልህ መንገድ ነው። የሚያደርገውም ልዩነቶችን ማጥፋት ሳይሆን ልዩነቶችን በአንድ ሀገር ጣሪያ ስር እንዴት እንደሚኖሩ የጋራ ሕግና ሥርዓት መፍጠር ነው። በእርግጥ ኢትዮጵያ ከባድ ፈተናዎችን አሳልፋለች። የፖለቲካ አለመተማመን፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የፀጥታ ችግሮች፣ የኢኮኖሚ ጫናዎችና የማኅበራዊ ስብራቶች በቀላሉ የሚያልፉ አይደሉም። ይሁን እንጂ እነዚህን ችግሮች በጥይት ከመፍታት ይልቅ በምክክር ለመፍታት መሞከር በራሱ የታሪክ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ ግን የአንድ ተቋም ብቻ አይደለም። የመንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኅን ተቋማት፣ የምሁራን፣ የወጣቶች፣ የሴቶችና የእያንዳንዱ ዜጋ የጋራ ኃላፊነት ነው። የሀገር ዕጣ ፋንታ ለአንድ ቡድን ብቻ የሚተው አይደለም፤ በጋራ የሚገነባ እንጂ። ከምክክር ወደ ባህል፡- ምክክሩ ተጠናቀቀ ማለት የሀገሪቱ ችግሮች ተፈቱ ማለት አይደለም። እውነተኛው ስኬት የሚለካው የመደማመጥ ባህል በማኅበረሰቡ ውስጥ ሲሰርጽ ነው። በትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በመገናኛ ብዙኅን፣ በፖለቲካ ተቋማትና በየቤቱ የመነጋገር ባህል ካልጠነከረ፣ ምክክሩ የሰነድ ውጤት ብቻ ሆኖ ይቀራል። የእውነተኛ ዴሞክራሲ መሠረት ተመሳሳይ አስተሳሰብ መኖር አይደለም፤ የተለያዩ አስተሳሰቦችን በሰላም የመቀበል ባህል መኖር ነው። ልዩነት የችግር ምንጭ ሳይሆን የጥንካሬ ምንጭ ሲሆን ነው አንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም የምታገኘው። የማጠቃለያ፡- የሀገራዊ ምክክር ሂደት የሚያስፈልገው ብልህ አመራር ብቻ አይደለም፤ ታጋሽ ዜጎችንም ይፈልጋል። ሀገር የምትገነባው በግንብ ሳይሆን በመተማመን ነው። ሰላም የሚጸናውም በፍርሃት ሳይሆን በፍትሕ ነው። ዛሬ የምንመርጠው የምክክር መንገድ ነገ ለልጆቻችን የምንተወው ታሪክ ይሆናል። ስለዚህ በኢትዮጵያን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተደራጅተው የሚመከርባቸው ስምንት ዐበይት አጀንዳዎች የዛሬ አጀንዳ ብቻ አይደሉም፤ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚቀርጽ የትውልድ አደራ እንጂ። የዋናው ምክክር ጉባኤ ተመካካሪ የሕዝብ ወኪሎችም ከግልና ቡድን ፍላጎት ይልቅ የቀጣዩን ትውልድና ሀገርን ማስቀደም ይጠበቅባቸውል። ምክክር የቃላት ልውውጥ ብቻ አይደለም፤ የተሰበረ መተማመንን የሚጠግን፣ የተከፋፈለ ማኅበረሰብን የሚያቀራርብ፣ የትውልድ ታሪክን በአዲስ ተስፋ የሚጽፍ ሀገራዊ ጥበብ ነው። የምንወስነው ዛሬ የምንወርሰውን ነገ ይበይናል። ምክክር የሀገር መድኅን ነው፤ ኢትዮጵያም እየመከረች ነው።
ፈተናዎችን ወደ ዕድል የቀየረው የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪው ዘርፍ እመርታ
Jul 21, 2026 499
በሙሴ መለሰ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሁለንተናዊ የፖሊሲና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ አዲስ መነቃቃትንና ተጨባጭ ስኬቶችን አስመዝግበዋል።መንግስት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ቀርፆ ወደ ተግባር በመግባት፣ የግል ዘርፉን በማበረታታት እና የአምራች ኢንዱስትሪውን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ከማመጣጠን ባለፈ፣ በሁሉም ንዑሳን የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ተስፋ እንዲፈነጥቅ አድርጓል። የለውጡ ዓመታት የኢንዱስትሪ ስኬቶች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ “ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገራዊ ንቅናቄ ነው። ይህ ንቅናቄ በፋይናንስ፣ በግብዓት እና በኃይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ሙሉ ማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ አድርጓል። ንቅናቄው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዓመታት ብቻ የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በርካታ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ የውጭ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የተቻለ ሲሆን፣በተለይም በጨርቃ ጨርቅ፣በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ እንዲሁም በምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል። ይህም የሀገሪቱን የአምራች ኢንዱስትሪ አማካይ የማምረት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፣ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን እንደ ኮሮና ወረርሽኝና የአጎዋ (AGOA) ስረዛ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችላለች። የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራን ጨምሮ በተቀረጹ ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አማካኝነት፣ ቀደም ሲል 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል። በተጨማሪም በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውንና ይህም የኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሂደትም እስካሁን ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3.6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን በወቅቱ ገልጸው ነበር። የኢትዮጵያን ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑት ተግባራት ሌላኛው የለውጡ ማሳያ ነው። በይርጋለም፣ቡሬ እና ቡልቡላ የሚገኙ የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሙሉ ስራ መግባት አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ለፋብሪካዎች እንዲያቀርብና እሴት የተጨመረበት ምርት ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንገድ ከፍቷል። ይህ ስትራቴጂ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራን ከማሳደጉም በላይ የኢንዱስትሪዎቹን የጥሬ ዕቃ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ እገዛ አድርጓል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኬሚካል፣ በፋርማሲዩቲካል እና በሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ማምረቻ ዘርፍ የታየው ስኬት ለሀገሪቱ የጤና ዋስትና ትልቅ ምሰሶ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ወጪ ከውጭ የሚገባ ሲሆን፣ በለውጡ ዓመታት ግን የአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች አቅም እንዲጎለብትና አዳዲስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የፋርማሲዩቲካል ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ ተደርጓል። ይህም ለአገር ውስጥ ገበያ ጥራት ያላቸው መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አስችሏል። በሌላ በኩል፣በኮንስትራክሽን እና ማዕድን ኢንዱስትሪ ላይ የታየው መነቃቃት የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመደገፍ አስችሏል። አዳዲስ የሲሚንቶ እና የብረት ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉ እና ነባሮቹ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ መደገፉ፣ በሀገሪቱ ለሚታዩት ሰፊ የኮሪደር ልማት እና የዘመናዊ ከተሞች ግንባታ ፕሮጀክቶች የአገር ውስጥ ግብዓትን በበቂ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏል። ማዕድናትን በተመለከተም፣ ጥሬ ግብአት ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ የመላክ ፖሊሲ በመተግበሩ የዘርፉን የሀገር ውስጥ ገቢ ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ለኢንዱስትሪው ዘርፍ መፋጠን ሌላው ዋነኛ አስደጋፊ የሆነው የኢነርጂ እና ታዳሽ ኃይል ልማት ዘርፍ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የውሃ፣ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቅና ወደ ሥራ መግባት አምራች ኢንዱስትሪዎች የሚያገኙትን የኃይል አቅርቦት እንዲያድግ አስችሏል። ይህ የአረንጓዴ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ (Eco-friendly) እንዲሆኑ አድርጓል። ከነዚህ ዘርፎች ባሻገር፣ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ሽግግር ተከትሎ በቴክኖሎጂው እና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የሞባይል ስልኮች እና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች የመገጣጠም ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።በተለይም ደግሞ ለአካባቢ ጥበቃና ለነዳጅ ወጪ ቅነሳ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) በአገር ውስጥ በስፋት መገጣጠም መጀመራቸው ሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ራሷን እንድትችል እና ለሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ዘላቂ የስራ ዕድል እንዲፈጠር መሰረት የጣለ እርምጃ ሆኗል። በአጠቃላይ፣ የለውጡ ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ውስጥ መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸው ነበሩ ሊባል ይችላል። ከፖሊሲ ማሻሻያ ጀምሮ እስከ መሬት ወርደው የተተገበሩ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ድረስ የተከናወኑት ተግባራት ሀገሪቱ በምርት ራሷን እንድትችል እና የውጭ ምርት ጥገኝነትን እንድትቀንስ አግዘዋታል። እነዚህ የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን የነገ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ጠንካራ መሰረቶች ናቸው።
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 4489
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 3611
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 10667
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 20863
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 13898
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 19651
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 6981
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 4802
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።