ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በተጠባቂው ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ከቶተንሃም ሆትስፐርስ ጋር አቻ ተለያየ
Feb 1, 2026 54
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐ-ግብር ቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ማንችስተር ሲቲ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን በማሸነፍ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ ማምሻውን በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ራያን ቸርኪ በ11ኛው እና አንቶዋን ሴሜንዮ በ44ኛው ደቂቃ ባስቆጠሯቸው ግቦች ማንችስተር ሲቲ 2 ለ 0 መምራት ችሎ ነበር። ከእረፍት መልስ ዶምኒክ ሶላንኬ በ53ኛው እና በ71ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋቸው ግቦች ቶተንሃምን አቻ አድርጓል። በመጀመሪያው አጋማሽ ማንችስተር ሲቲ፣ በሁለተኛው አጋማሽ ቶተንሃም ሆትስፐርስ የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገዋል። የ2 ለ 0 መሪነቱን ማስጠበቅ ያልቻለው ማንችስተር ሲቲ በ47 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ጥሏል። ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ከአራት ወደ ስድስት ከፍ ብሏል። ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ29 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ የዛሬውን ጨምሮ ባለፉት ስድስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ዛሬ በተደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን 3 ለ 2 ሲያሸንፍ ብሬንትፎርድ አስቶንቪላን 1 ለ 0 ረቷል። ኖቲንግሃም ፎረስት እና ክሪስታል ፓላስ አንድ አቻ ተለያይተዋል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ነገ ሰንደርላንድ እና በርንሌይ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል።
የሀገር ውስጥ ገበያውን ለማረጋጋት የሚጥሩ ፋብሪካዎች ሀገራዊ አበርክቷቸው ቀላል አይደለም-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Feb 1, 2026 43
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ የሀገር ውስጥ ገበያውን ለማረጋጋት የሚጥሩ ፋብሪካዎች ሀገራዊ አበርክቷቸው ቀላል የሚባል አይደለም ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አስገነዘቡ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ የሚገኘውን አማጋ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካን መጎብኘታቸውን ገልጸዋል። በቅርቡ ወደ ሥራ የገባው ፋብሪካው፤ ተከላው ሙሉ በሙሉ በቅርቡ ሲጠናቀቅ በዋናነት ብርድ ልብስ፣ የአልጋ ልብስ፣ የሶፋ ልብስ፣ መጋረጃ፣ የአንሶላ ጨርቅ፣ ጂንስ እና ሁሉንም አይነት የጨርቃ ጨርቅ ምርቶች በተለየዩ ዲዛይኖች እና ልኬት ማምረት ያስችለዋል ብለዋል። ጥራት ያላቸው ተኪ ምርቶችን የሚያመርቱና በቀጥታ ምርቶችን ለውጭ ገበያ ከማቅረብ ይልቅ፤ የሀገር ውስጥ ገበያውን ለማረጋጋት የሚጥሩ ፋብሪካዎች ሀገራዊ አበርክቷቸው ቀላል የሚባል አይደለም ሲሉም አስገንዝበዋል።
ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሶስተኛ ከፍ አደረገ
Feb 1, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ18ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ከቤ ብዙነህ በጨዋታ እና ዳዊት ተፈራ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ነገሌ አርሲ በ32 ነጥብ ደረጃውን ከአራተኛ ወደ ሶስተኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ዘጠነኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በሊጉ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ20 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ተጠባቂ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 አሸንፏል። የቅዱስ ጊዮርጊሱ ቶሎሳ ንጉሴ በ82ኛው ደቂቃ በራሱ ላይ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በውድድር ዓመቱ ስምንተኛ ድሉን ያስመዘገበው ፋሲል ከነማ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ32 ነጥብ ከነበረበት አምስተኛ ደረጃ ወደ አራተኛ ከፍ ብሏል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ለሰባተኛ ጊዜ የተሸነፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ23 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት ሶስት ተከታታይ ጨዋታዎች አላሸነፈም። በሌላኛው መርሐ-ግብር መቀሌ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። የኢትዮጵያ ቡናው በፍቃዱ አለማየሁ በራሱ ላይ ለመቀሌ 70 እንደርታ፣ አምበሉ ራምኬል ጀምስ ለኢትዮጵያ ቡና ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። መቀሌ 70 እንደርታ በ18 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ኢትዮጵያ ቡና በ20 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ቀን ላይ በተደረገ የመጀመሪያ ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 በመርታት በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 18ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ19ኛ ሳምንት እና የሊጉ የመጀመሪያ ዙር የማጠናቀቂያ መርሐ-ግብር ከጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
ለአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የጤና አገልግሎትን ተደራሽነት ለማሳካት ለጤና መድህን አገልግሎት ትኩረት ተሰጥቷል
Feb 1, 2026 90
ሰመራ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የጤና አገልግሎትን ተደራሽነትና ጥራት ለማሳካት ለጤና መድህን አገልግሎት ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ። በኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት የአፋር ክልል ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀምና የቀጣይ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መሐመድ ሁሴን እንደተናገሩት፤ በክልሉ የህብረተሰብ ጤና አገልግሎትን ተደራሽነትና ጥራት ለማሳካት ለጤና መድህን አገልግሎት ትኩረት ተሰጥቷል። ለዚህም በክልሉ ባሉ ሁሉም ወረዳዎች አገልግሎቱን ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊው እገዛ እንደሚደረግ ጠቁመዋል። የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኀላፊ አቶ ዊቲካ ኖሬ በበኩላቸው፤ የክልሉን ማህበረሰብ የጤና አገልግሎት ጥራትና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በቅንጅት መሰራቱን አንስተዋል። ተግባሩን በማጠናከር የጤና አገልግሎቱን ውጤታማ ለማድረግ አሰራሩን የማዘመንና የጤና መድህን አገልግሎትን ለማስፋፋት መሰራቱን ተናግረዋል። በዚህም በክልል ደረጃ የተጠቃሚ አባዎራዎችና እማዎራዎችን ቁጥር ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የአመራሩን ቁርጠኝነት እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ያምሮት አንዷለም እንዳሉት፤ እንደ ሀገር የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎትን ፍትሃዊነትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው። በአፋር ክልልም አገልግሎቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ መረጃዎች በአንድ ቋት ውስጥ የማካተት ስራ መከናወኑን ጠቁመዋል። በክልሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ያልሆኑ ወረዳዎችን ወደ ስራው ለማካተት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። በመድረኩ የአፋር ክልል ከፍተኛ የስራ ኀላፊዎችና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።
ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን በማሸነፍ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ
Feb 1, 2026 57
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በ24ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን 3 ለ 2 በመርታት ደረጃውን ከነበረበት ወደ አራተኛ ከፍ ያደረገ ሲሆን ሶስተኛ ተከታታይ ድሉንም አስመዝግቧል። የማንችስትር ዩናይትድን ግቦች ካስሚሮ በ19ኛው፣ ኩና በ56ኛው እንዲሁም ሴስኮ በ94ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፈዋል። በአንጻሩ ሂምኔዝ በ85ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት እና ኬቪን በ92ኛው ደቂቃ በጨዋታ ለፉልሃም ግቦችን አስቆጥረዋል። ውጤቱን ተከትሎም ማንችስተር ዩናይትድ በ41 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ዳግም የተረከበ ሲሆን፤ ፉልሃም በ34 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሌላ የጨዋታ መርሐ-ግብር ብሬንትፎርድ አስቶንቪላን በሜዳው 1 ለ 0 ሲያሸንፍ፤ ኖቲንግሃም ከክሪስታል ፓላስ አንድ አቻ ተለያይተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ፖለቲካ
ፓርቲው በክልሉ የፖለቲካና የአደረጃጀት ስራዎችን በብቃት በመምራት የላቀ ውጤት አስመዝግቧል
Feb 1, 2026 80
ቦንጋ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ፓርቲው የፖለቲካና የአደረጃጀት ስራዎችን በብቃት በመምራት በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ተናገሩ፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ በመደረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት፣ ፓርቲው በሀገርም ሆነ በክልል ደረጃ ለውጡን በመምራት አሻጋሪ ተግባራትን በቅንጅት እየሰራ ነው። ለዚህም ዘርፈ ብዙ ሪፎርሞችን በመተግበር የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋትና ተተኪ አመራር ለመፍጠር ትኩረት መስጠቱን ተናግረዋል። በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ፣ በዲሞክራሲ ባህል ግንባታና በሌሎችም ዘርፎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። የሰለጠነ የፖለቲካ ስርአት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ለአባላቱና ደጋፊዎቹ ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ በማድረግ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አንስተዋል። የፖለቲካና የአደረጃጀት ስራዎችን በብቃት በመምራት በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች የላቀ ውጤት መምጣቱን ጠቁመዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ተአማኒና ነፃ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ፓርቲው ሚናውን እንደሚወጣ ተናግረዋል። በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የስትራቴጂክ ስራ አመራር ዘርፍ ሀላፊ አቶ አንተነህ አየለ፤ የስድስት ወራት አፈፃፀም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት፣ የአባላቱንና አመራሩን አቅም በማሳደግና በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ አንስተዋል። የፓርቲውን አመራርና አባላትን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ለመፍጠር የተደረጉ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ያመጡትን ለውጥ ለማስቀጠል እንደሚሰራም አመልክተዋል። የዴሞክራሲ ባህል ግንባታን ለማጠናከር በሚደረገው ጥረትም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና አባላት የህግና የፓርቲ ስነምግባር መመሪያን ይበልጥ እንዲያክብሩ በጥብቅ ዲሲፕሊን መመራቱን አንስተዋል። በመድረኩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማንን ጨምሮ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የፓርቲው ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ምርታማነትን በማሳደግ የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል
Feb 1, 2026 63
ባሕር ዳር፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በሁሉም ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል አመራሩ ሕዝባዊ ንቅናቄ በመፍጠር ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅበት የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አስገነዘቡ። የክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎች ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት በሁሉም ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን በዚሁ ወቅት ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ተናግረዋል። ለዚህም ክልሉ የ25 ዓመት አሻጋሪና ዘላቂ የልማት ዕቅድና የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በተሻለ ሁኔታ እየተገበረ መሆኑን አስታውቀዋል። ለአብነትም በሰብል ልማት፣ በእንስሳት፣ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እና መሰል ሥራዎች ሞዴል የሆኑና ይበልጥ ሊሰፉ የሚችሉ ውጤቶችን ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል። በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ የአገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻልና በሌሎች ዘርፎችም የተሻለ ዕድገት ማስመዝገብ መቻሉን ነው ያመለከቱት። ችግሮችን በመቋቋም የተገኙ ውጤቶች የሚበረታቱ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ አሁንም የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ዘላቂነት ማረጋገጥ እንደሚገባ በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ የተገኙ ውጤቶችን ማስፋት ይገባል ነው ያሉት። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ በኩል አመራሩ ሕዝቡን በነቂስ በማነቃነቅ በጋራ መረባረብ እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል። በቀሪ ወራትም በየዘርፎቹ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ ትብብርን በማጠናከር መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተለይም በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የኑሮ ውድነትን በመፍታትና የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ የተለየ ትኩረት ተሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ ርዕሰ መሥተዳድሩ ተናግረዋል። በመድረኩ ጥንካሬዎችንና ድክመቶችን በጥልቀት በመመልከት የቀጣይ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ሊቀመጡ ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያ የቀጣናዊ ብልጽግና ሞተር እና የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ናት- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Feb 1, 2026 87
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- ከሕልም ወደ እውነት፤ ኢትዮጵያ የቀጣናዊ ብልጽግና ሞተር እና የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ናት ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ባወጣው መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስና ብሩኅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ብሏል። ትናንት ስናልማቸው የነበሩ ታላላቅ ርዕዮች ዛሬ በተግባር ተተርጉመው የዜጎች ተጠቃሚነት የሚረጋገጥባቸው፣ የሀገር ክብር የሚታደስባቸውና የቀጣናው ትስስር የሚጠናከርባቸው ኅያው እውነታዎች ሆነዋል ሲልም ገልጿል። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡- "ከሕልም ወደ እውነት፡ ኢትዮጵያ የቀጠናዊ ብልፅግና ሞተር እና የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል!” የኢፌድሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጥር 24 /2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስና ብሩህ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት ስናልማቸው የነበሩ ታላላቅ ርዕዮች ዛሬ በተግባር ተተርጉመው የዜጎች ተጠቃሚነት የሚረጋገጥባቸው፣ የሀገር ክብር የሚታደስባቸውና የቀጠናው ትስስር የሚጠናከርባቸው ህያው እውነታዎች ሆነዋል። በትናንትናው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት፣ የቀጠናው ሀገራት መሪዎች በተገኙበት የተመረቁት ግዙፍ ፕሮጀክቶች፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት የመሆን ህልሟን ለማሳካት የያዘችው ጽኑ አቋም ማሳያ ናቸው። ይህ ታሪካዊ ዕለት ኢትዮጵያ በአንድ በኩል የታዳሽ ኃይል ሉዓላዊነቷን የምታረጋግጥበትን የአይሻ-2 የንፋስ ኃይል ማመንጫን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የቱሪዝም ዘርፉንና የባህል እሴቶቻችንን ከፍ የሚያደርገውን የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውን የሸበሌ ሪዞርትን ለዓለም ያስተዋወቀችበት አጋጣሚ ነው። እነዚህ ተግባራት የመደመር እሳቤ ያዋለዳቸው ከሕልም ወደ እውነት የተሸጋገሩ የኢትዮጵያ ማንሰራራት ምልክቶችና የምሥራቅ አፍሪካ የጋራ ልማት ዋስትናዎች ናቸው። ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው ትልቁ ድል ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው መመረቃቸው አይደለም፣ ፕሮጀክት ጀምሮ መጨረስ የዕለት ተዕለት ተግባራችንና መለያችን ሆኗል። ይልቁንም ይበልጥ የሚያስደምመው ሀገሪቱ ከአንድ ግዙፍ ፕሮጀክት ወደ ሌላ ታላላቅ ፕሮጀክቶች የምትሸጋገርበት ፍጥነት፣ ቅልጥፍ እና የማላቅ አቅም ነው፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ ታላላቅ ርዕዮችን አልሞ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ተግባር የመለወጥ ብቃት ያለው ትጉህ አመራርና ከእያንዳንዱ የለውጥ ጉዞ ጎን የተሰለፈ ቆራጥ ህዝብ ያላት ሀገር መሆኗን በተግባር አስመስክራለች። ሰርክ በእያንዳንዱ እለት የሚበሰሩ ውጤቶች፣ ኢትዮጵያ ማንኛውንም ውስብስብ እና ግዙፍ ሥራ የማስተባበርና የመምራት አቅም እንደፈጠረች ማሳያ ናቸው። የጀመርነውን የመጨረስና የቋጨነውን ደግሞ ለቀጣይ ትውልድ በቅርስነት የማስተላለፍ ባህል በሀገራችን እየተገነባ መምጣቱ ለነገዋ ኢትዮጵያ ታላቅ ተስፋን ሰንቋል። በእነዚህ ፕሮጀክቶች ምረቃ ላይ የቀጠናችን ሀገራት መሪዎች በጋራ መገኘታቸው ፋይዳው ከፍተኛ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የምታከናውናቸው የልማት ሥራዎች ሁሉ ከራሷ አልፈው ለጎረቤቶቿ የሚተርፉና ቀጠናውን በጋራ ተጠቃሚነት የሚያስተሳስሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይታለች። የአይሻ-2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ በምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የንፋስ ኮሪደር ላይ መገንባቱ፣ ኢትዮጵያ የቀጠናው የታዳሽ ኃይል ማዕከል የመሆን ጉዞዋን የሚያፋጥን ታሪካዊ ክስተት ነው። ይህ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለሀገራችን ኢንዱስትሪዎች ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጠናው ሀገራት የኢኮኖሚ ትስስር የጀርባ አጥንት ነው። በቴክኖሎጂ ለሚመራና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለሚታገዝ ዘመናዊ ኢኮኖሚ ወሳኝ የሆነው ይህ መሰረተ-ልማት፣ በሕዝቦች መካከል ያለውን ወንድማማችነት የሚያጠናክር የሰላም ድልድይ ሆኖ ያገለግላል። ኢትዮጵያ ኃይልን በማመንጨትና ለአጎራባች ሀገራት በማከፋፈል፣ የቀጠናው የኢኮኖሚ ሞተር የመሆን ሚናዋን ቃልን በተግባር በመፈጸም እየተወጣች ትገኛለች። ሀገራችን ዛሬ ከወንዞቻችን፣ ከንፋስና ከምድር ውስጥ እንፋሎት በምታመነጨው ንጹህ ኃይል በአለም አቀፍ ደረጃ የአረንጓዴ ልማት መሪ እየሆነች መጥታለች። እነዚህ ስራዎች የኃይል ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ፣ ለአለም የበካይ ጋዞችን የመከላከል ጉዞ የበኩሏን ጉልህ አስተዋፅኦ ያሳየችበት አውድ ነው። በተመሳሳይ መልኩ የሸበሌ ሪዞርት ባህላዊ እሴቶቻችንን ከዘመናዊነት ጋር አቀናጅቶ፣ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ ያላትን ሰፊ አቅም ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የመለወጥ ብቃቷን ያሳየበት የ‘ገበታ ለትውልድ’ ድንቅ ውጤት ነው። በአጠቃላይ ትላንት በሰላም እጦት ይታወቁ የነበሩ አካባቢዎች ዛሬ የልማት ተምሳሌት መሆናቸው፣ ሀገራችን እየገነባች ያለቸው ሰላም ለልማት ማገር መሆኑን ያረጋግጣል። ኢትዮጵያ የምታልም ብቻ ሳትሆን ሕልሟን ወደ እውነት የምትቀይር፣ የቀጠናውን የልማት ተስፋ የምታለመልምና የአፍሪካ ኩራት ሆና የምትቀጥል ቆራጥ ሀገር ናት። ትላንት የተመረቁት ፕሮጀክቶች የነገዋን ብልፅግና የምናረጋግጥባቸው ኩሩ ቅርሶቻችን ናቸው። መንግሥት ከቀጠናው ሀገራት ጋር በመሆን ለጋራ ብልፅግና የሚተጋበትን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል። ህዝባችንም ይህንን የታሪክ እጥፋት በአግባቡ በመረዳትና ለላቀ ሥራ በመነሳሳት የሀገራችንን ከፍታ እንዲያረጋግጥ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ኢትዮጵያ በቀጠናው የብልፅግና ጮራ፣ በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ሆና መዝለቋን ትቀጥላለች! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! የኢፌድሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጥር 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
የሐሳብ የበላይነትን መሠረት ያደረገ ውድድር ለማካሄድ መዘጋጀታቸውን ፓርቲዎች ገለጹ
Feb 1, 2026 73
ወልቂጤ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የሐሳብ የበላይነትን መሠረት ያደረገ ውድድር ለማካሄድ መዘጋጀታቸውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አመራርና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ደምስ ገብሬ፤ መጪው ምርጫ የሐሳብ የበላይነት ጎልቶ የሚወጣበት እንዲሆን እንሠራለን ብለዋል። ፓርቲው በምርጫው የተሻለ ሐሳብ ይዞ በመቅረብና በፖሊሲ አማራጮች ላይ ክርክሮችና ፉክክሮችን በማድረግ የሕዝብ ይሁንታ ለማግኘት በቂ ዝግጅት እያደረገ መሆኑንም ለኢዜአ ተናግረዋል። ለዘላቂ ሰላም፣ ልማትና የሕግ የበላይነት መስፈን በሐሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ አካሄድ መከተል አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ፓርቲው ፍትሐዊ ምርጫ እንዲካሔድ የድርሻውን ከመወጣት ባለፈ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ሥርዓት መጠናከር የሚጠበቅበትን ሚና ይወጣል ብለዋል። የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባልና በብልጽግና ፓርቲ የጉራጌ ዞን ተወካይ ሔኖክ አብዱልሰመድ በበኩላቸው፤ ምርጫው ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። ምርጫው የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል የሚታይበት እንዲሆንም ፓርቲው ያላሰለ ጥረት እንደሚያደርግ አማላክተዋል። ፓርቲያቸው የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ሊቀይሩ በሚችሉ ተጨባጭ ጉዳዮች ላይ በማተኮር እንደሚወዳደር ያስታወቁት ደግሞ በእናት ፓርቲ የጉራጌ ዞን አካባቢ ሰብሳቢ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ፀሐፊ እንዳለ ኤርጌዶ ናቸው። የምርጫ ውድድሩ በፖሊሲ አማራጮችና በሐሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን እየሠሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል። በጋራ ምክር ቤቱ የሚገኙ ሁሉም ፓርቲዎች ለምርጫው ስኬታማነት፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የበኩላቸውን ለመወጣት እየሠሩ መሆኑም ነው የተገለጸው።
ለምርጫው ሂደት መሳካት የዜጎች ተሳትፎ እንዲጎለብት የሚጠበቅብንን ኃላፊነት እንወጣለን -የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች
Jan 31, 2026 90
ሀዋሳ፤ ጥር 23/2018(ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምርጫው መሳካት የዜጎች ተሳትፎ እንዲጎለብት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት እየሰሩ መሆኑን በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለፁ፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ በቁጥር 1113/2011 የመንግሥት አሠራር በግልጽነት፣ በተጠያቂነትና በአሳታፊነት እንዲከናወን ለማድረግ የነቃና በነፃነት የተደራጀ ማኅበረሰብ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን በማመን ሊወጣ ችሏል። በአገሪቱ ልማትና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸው ሚና እንዲጎለብት ለማድረግ እና የተመቻቸ ምህዳር ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን በመረዳትም አዋጁ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ወጥቷል። በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችም ዘንድሮ የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ሠላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ለኢዜአ ገልፀዋል፡፡ የኢየሩሳሌም የሕፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የሀዋሳና አካባቢው ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ማስረሻ ክብረት ምርጫ ዜጎች የመምረጥና የመመረጥ መብታቸውን በተሳትፎ የሚያረጋግጡበት የዴሞክራሲ ባህል መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዴሞክራሲ ሊጎለብት የሚችለው ደግሞ የምርጫ ሂደቱ ሠላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ይዘት ሲኖረው እንደሆነ ጠቅሰው ሁላችንም ለዚህ ስኬት የበኩላችንን ጥረት ማድረግ አለብን ብለዋል፡፡ ድርጅታቸው ከእድሮች፣ ከሴቶችና ወጣት ማህበራት ጋር እንደሚሰራ ገልፀው በነዚህ ተቋማት አማካኝነት ህብረተሰቡ በሀገራዊ ምርጫው ንቁ ተሳትፎ እንዲኖረው ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የ“ሻይኒ ዴይ” የማህበረሰብ ልማት አገልግሎት ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጌታቸው ዘውዴ (ዶ/ር) በበኩላቸው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ ሂደት ውስጥ ማህበረሰቡ መብትና ግዴታውን አውቆ በመምረጥም ሆነ በመመረጥ መሳተፍ እንዲችል የግንዛቤ ስራ ይሰራሉ ብለዋል፡፡ ድርጅታቸው ዜጎች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድህረ ምርጫ ወቅት ሊያከናውኗቸው የሚችሉትንና ማከናወን ያለባቸውን ዝርዝር ጉዳዮች የማስገንዘብ ፈቃድ ከምርጫ ቦርድ ማግኘቱንም ጠቁመዋል፡፡ ድርጅታቸው በተለይም ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞችና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎችን ማዕከል አድርጎ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እንደሚሰራ የገለፁት ደግሞ የ“ሴንተር ኦፍ ኮንሰርን” ፕሮግራም ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳንኤል ግዛቸው ናቸው፡፡ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሻለ ግንዛቤ ኖሯቸው በተሻለ መንገድ እንዲሳተፉ በማድረግ የምርጫ ሂደቱ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሰሩ እንደሚገኙ ነው የተናገሩት፡፡
ቦርዱ እያከናወናቸው ያሉ የሕግና የአሠራር ሥርዓት ማሻሻያዎች ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር በኩል ከፍተኛ ድርሻ አላቸው
Jan 30, 2026 134
አዲስ አበባ፤ ጥር 22/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እያከናወናቸው ያሉ የሕግና የአሠራር ሥርዓት ማሻሻያዎች ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ይበልጥ ዴሞክራሲያዊነት ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር በኩል ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ፡፡ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሐሳብ የበላይነት እና በሕዝብ ይሁንታ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲካሄድ የጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱ ይታወሳል። በዚህም የዕጩዎች ምዝገባ ከጥር 1 እስከ የካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሁም የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ይከናወናል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ምርጫው ሰላማዊና ስኬታማ እንዲሆን ምክር ቤቱ ልዩ ዕቅድ አውጥቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ሰፊ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቅሰው፣ ለዚህም በቢሾፍቱ የተደረሰው የሰላም ቃል ኪዳን እንደ ትልቅ ስኬት እንደሚጠቀስ አስረድተዋል። ምርጫው ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን መንግስት እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎችን አድንቀው፣ በተለይም በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀው የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ማሻሻያ አዋጅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የአዋጁ መሻሻል ችግሮችን በንግግር መፍታት እንደሚቻል ያሳየና ለነፃ ምርጫ ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነውም ብለዋል። በተጨማሪም የዘንድሮውን የዕጩዎች ምዝገባ ለየት የሚያደርገው በዲጂታል ዘዴ መከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም የሀገሪቱን የቴክኖሎጂ ጉዞ የሚያግዝ መሆኑን አብራርተዋል። 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሀገሪቱ በብሔራዊ ምክክር እና በፖለቲካዊ መረጋጋት ሂደት ውስጥ ባለችበት ወቅት መከናወኑ ትልቅ ትርጉም አለው ብለዋል። ሰላምና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የማይነጣጠሉ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ሰለሞን፣ ሁሉም ፓርቲዎች ሕግና ሥርዓትን አክብረው መንቀሳቀስ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ለትውልድ የሚተላለፍ ጠንካራ ሀገር እና ነፃ የዴሞክራሲ ባህል መገንባት የሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ኃላፊነት መሆኑንም ነው የተናገሩት። ምክር ቤቱ ምርጫው ፍፁም ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ከመንግስት ጋር በቅንጅት መስራቱን እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በክልሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተሰጡ አቅጣጫዎች መሰረት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ፍጥነትና ፈጠራን መሰረት ባደረገ መልኩ ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jan 30, 2026 141
አዲስ አበባ፤ ጥር 22/2018(ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተሰጡ አቅጣጫዎች መሰረት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ፍጥነትና ፈጠራን መሰረት ባደረገ መልኩ እናስቀጥላለን ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች በመደመር መንግሥት እይታ የዘርፎች እመርታ ሥልጠና ማጠቃለያ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተሰጡ አቅጣጫዎች ግቦች አፈፃፀም ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱም አቶ ጌቱ ወዬሳ እንዳሉት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተሰጡ አቅጣጫዎች መሰረት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት በውጤታማነት እንዲቀጥሉ አመራሩ በቁርጠኝነት ይሰራል። በክልሉ በተለይም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ፤ የቅዳሜ እና የእሁድ ገበያን በማስፋፋት አምራችና ሸማችን በማገናኘት እንዲሁም የቁጥጥርና ክትትል ስራዎች በማጠናከር የኑሮ ውድነት ለመቀነስ እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል። የዲጂታላይዜሽን አሰራሮችን በማሳደግ እንዲሁም ተጠያቂነትን በማስፈን፤ የሰላም እሴት ግንባታ ስራዎች የማሳደግ እንዲሁም ጠባቂነትን ለመቀነስ እየተደረጉ የሚገኙ ርብርቦችን አጠናክረን እናስቀጥላለን ነው ያሉት። ለአርሶ አደሩ ተገቢውን ድጋፍ በማድረግ በክልሉ የሚታረስ መሬት ፆሙን እንዳያድር የማድረግ፤ በምግብ ራስን ለመቻልና ከተረጂነት ለመላቀቅ እንዲሁም ኮንትሮባንድንና የመሬት ወረራንና ህገወጥ ግንባታን ዜሮ ለማድረግ የሚሰሩ ስራዎች የበለጠ ይጠናከራሉ ብለዋል። የገጠር ኮሪደር፣ የምርት ማከማቻ ግንባታን የማፋጠን፣ የሽያጭ ማዕከልና አግሮ ፕሮሰሲንግ ግንባታ እንዲሁም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማስፋት እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ፍጥነትና ፈጠራ በታከለበት መልኩ እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። የሌማት ትሩፋትን በማስፋት፣ የበጋ እርሻና የኩታ ገጠም ስራዎችን የማሳደግ እንዲሁም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማሳደግ፤ ለኢንቨስትመንት ዘርፉ ተገቢው ድጋፍ በማድረግ እንዲጎለብት ማስቻል፤ የማዕድን ዘርፉ ላይ ያሉ ሀብቶችን ለመጠቀም የሚሰሩ ስራዎች እንዲሁ ይጠናከራሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን በማጠናከር ኢንዱስትሪዎችን የማሳደግ ስራ ላይም እየተሰሩ የሚገኙ ጅምር ስራዎችን ለማሳደግም ትኩረት ተደርጓል ብለዋል። የተቀመጡ አቅጣጫዎች ተግባራዊ ስለመሆናቸው የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰራም ነው አቶ ጌቱ ያስገነዘቡት።
ፖለቲካ
ፓርቲው በክልሉ የፖለቲካና የአደረጃጀት ስራዎችን በብቃት በመምራት የላቀ ውጤት አስመዝግቧል
Feb 1, 2026 80
ቦንጋ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ፓርቲው የፖለቲካና የአደረጃጀት ስራዎችን በብቃት በመምራት በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ተናገሩ፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ በመደረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት፣ ፓርቲው በሀገርም ሆነ በክልል ደረጃ ለውጡን በመምራት አሻጋሪ ተግባራትን በቅንጅት እየሰራ ነው። ለዚህም ዘርፈ ብዙ ሪፎርሞችን በመተግበር የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋትና ተተኪ አመራር ለመፍጠር ትኩረት መስጠቱን ተናግረዋል። በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ፣ በዲሞክራሲ ባህል ግንባታና በሌሎችም ዘርፎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። የሰለጠነ የፖለቲካ ስርአት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ለአባላቱና ደጋፊዎቹ ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ በማድረግ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አንስተዋል። የፖለቲካና የአደረጃጀት ስራዎችን በብቃት በመምራት በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች የላቀ ውጤት መምጣቱን ጠቁመዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ተአማኒና ነፃ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ፓርቲው ሚናውን እንደሚወጣ ተናግረዋል። በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የስትራቴጂክ ስራ አመራር ዘርፍ ሀላፊ አቶ አንተነህ አየለ፤ የስድስት ወራት አፈፃፀም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት፣ የአባላቱንና አመራሩን አቅም በማሳደግና በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ አንስተዋል። የፓርቲውን አመራርና አባላትን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ለመፍጠር የተደረጉ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ያመጡትን ለውጥ ለማስቀጠል እንደሚሰራም አመልክተዋል። የዴሞክራሲ ባህል ግንባታን ለማጠናከር በሚደረገው ጥረትም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና አባላት የህግና የፓርቲ ስነምግባር መመሪያን ይበልጥ እንዲያክብሩ በጥብቅ ዲሲፕሊን መመራቱን አንስተዋል። በመድረኩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማንን ጨምሮ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የፓርቲው ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ምርታማነትን በማሳደግ የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል
Feb 1, 2026 63
ባሕር ዳር፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በሁሉም ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል አመራሩ ሕዝባዊ ንቅናቄ በመፍጠር ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅበት የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አስገነዘቡ። የክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎች ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት በሁሉም ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን በዚሁ ወቅት ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ተናግረዋል። ለዚህም ክልሉ የ25 ዓመት አሻጋሪና ዘላቂ የልማት ዕቅድና የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በተሻለ ሁኔታ እየተገበረ መሆኑን አስታውቀዋል። ለአብነትም በሰብል ልማት፣ በእንስሳት፣ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እና መሰል ሥራዎች ሞዴል የሆኑና ይበልጥ ሊሰፉ የሚችሉ ውጤቶችን ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል። በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ የአገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻልና በሌሎች ዘርፎችም የተሻለ ዕድገት ማስመዝገብ መቻሉን ነው ያመለከቱት። ችግሮችን በመቋቋም የተገኙ ውጤቶች የሚበረታቱ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ አሁንም የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ዘላቂነት ማረጋገጥ እንደሚገባ በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ የተገኙ ውጤቶችን ማስፋት ይገባል ነው ያሉት። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ በኩል አመራሩ ሕዝቡን በነቂስ በማነቃነቅ በጋራ መረባረብ እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል። በቀሪ ወራትም በየዘርፎቹ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ ትብብርን በማጠናከር መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተለይም በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የኑሮ ውድነትን በመፍታትና የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ የተለየ ትኩረት ተሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ ርዕሰ መሥተዳድሩ ተናግረዋል። በመድረኩ ጥንካሬዎችንና ድክመቶችን በጥልቀት በመመልከት የቀጣይ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ሊቀመጡ ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያ የቀጣናዊ ብልጽግና ሞተር እና የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ናት- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Feb 1, 2026 87
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- ከሕልም ወደ እውነት፤ ኢትዮጵያ የቀጣናዊ ብልጽግና ሞተር እና የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ናት ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ባወጣው መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስና ብሩኅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ብሏል። ትናንት ስናልማቸው የነበሩ ታላላቅ ርዕዮች ዛሬ በተግባር ተተርጉመው የዜጎች ተጠቃሚነት የሚረጋገጥባቸው፣ የሀገር ክብር የሚታደስባቸውና የቀጣናው ትስስር የሚጠናከርባቸው ኅያው እውነታዎች ሆነዋል ሲልም ገልጿል። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡- "ከሕልም ወደ እውነት፡ ኢትዮጵያ የቀጠናዊ ብልፅግና ሞተር እና የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል!” የኢፌድሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጥር 24 /2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስና ብሩህ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት ስናልማቸው የነበሩ ታላላቅ ርዕዮች ዛሬ በተግባር ተተርጉመው የዜጎች ተጠቃሚነት የሚረጋገጥባቸው፣ የሀገር ክብር የሚታደስባቸውና የቀጠናው ትስስር የሚጠናከርባቸው ህያው እውነታዎች ሆነዋል። በትናንትናው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት፣ የቀጠናው ሀገራት መሪዎች በተገኙበት የተመረቁት ግዙፍ ፕሮጀክቶች፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት የመሆን ህልሟን ለማሳካት የያዘችው ጽኑ አቋም ማሳያ ናቸው። ይህ ታሪካዊ ዕለት ኢትዮጵያ በአንድ በኩል የታዳሽ ኃይል ሉዓላዊነቷን የምታረጋግጥበትን የአይሻ-2 የንፋስ ኃይል ማመንጫን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የቱሪዝም ዘርፉንና የባህል እሴቶቻችንን ከፍ የሚያደርገውን የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውን የሸበሌ ሪዞርትን ለዓለም ያስተዋወቀችበት አጋጣሚ ነው። እነዚህ ተግባራት የመደመር እሳቤ ያዋለዳቸው ከሕልም ወደ እውነት የተሸጋገሩ የኢትዮጵያ ማንሰራራት ምልክቶችና የምሥራቅ አፍሪካ የጋራ ልማት ዋስትናዎች ናቸው። ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው ትልቁ ድል ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው መመረቃቸው አይደለም፣ ፕሮጀክት ጀምሮ መጨረስ የዕለት ተዕለት ተግባራችንና መለያችን ሆኗል። ይልቁንም ይበልጥ የሚያስደምመው ሀገሪቱ ከአንድ ግዙፍ ፕሮጀክት ወደ ሌላ ታላላቅ ፕሮጀክቶች የምትሸጋገርበት ፍጥነት፣ ቅልጥፍ እና የማላቅ አቅም ነው፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ ታላላቅ ርዕዮችን አልሞ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ተግባር የመለወጥ ብቃት ያለው ትጉህ አመራርና ከእያንዳንዱ የለውጥ ጉዞ ጎን የተሰለፈ ቆራጥ ህዝብ ያላት ሀገር መሆኗን በተግባር አስመስክራለች። ሰርክ በእያንዳንዱ እለት የሚበሰሩ ውጤቶች፣ ኢትዮጵያ ማንኛውንም ውስብስብ እና ግዙፍ ሥራ የማስተባበርና የመምራት አቅም እንደፈጠረች ማሳያ ናቸው። የጀመርነውን የመጨረስና የቋጨነውን ደግሞ ለቀጣይ ትውልድ በቅርስነት የማስተላለፍ ባህል በሀገራችን እየተገነባ መምጣቱ ለነገዋ ኢትዮጵያ ታላቅ ተስፋን ሰንቋል። በእነዚህ ፕሮጀክቶች ምረቃ ላይ የቀጠናችን ሀገራት መሪዎች በጋራ መገኘታቸው ፋይዳው ከፍተኛ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የምታከናውናቸው የልማት ሥራዎች ሁሉ ከራሷ አልፈው ለጎረቤቶቿ የሚተርፉና ቀጠናውን በጋራ ተጠቃሚነት የሚያስተሳስሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይታለች። የአይሻ-2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ በምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የንፋስ ኮሪደር ላይ መገንባቱ፣ ኢትዮጵያ የቀጠናው የታዳሽ ኃይል ማዕከል የመሆን ጉዞዋን የሚያፋጥን ታሪካዊ ክስተት ነው። ይህ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለሀገራችን ኢንዱስትሪዎች ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጠናው ሀገራት የኢኮኖሚ ትስስር የጀርባ አጥንት ነው። በቴክኖሎጂ ለሚመራና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለሚታገዝ ዘመናዊ ኢኮኖሚ ወሳኝ የሆነው ይህ መሰረተ-ልማት፣ በሕዝቦች መካከል ያለውን ወንድማማችነት የሚያጠናክር የሰላም ድልድይ ሆኖ ያገለግላል። ኢትዮጵያ ኃይልን በማመንጨትና ለአጎራባች ሀገራት በማከፋፈል፣ የቀጠናው የኢኮኖሚ ሞተር የመሆን ሚናዋን ቃልን በተግባር በመፈጸም እየተወጣች ትገኛለች። ሀገራችን ዛሬ ከወንዞቻችን፣ ከንፋስና ከምድር ውስጥ እንፋሎት በምታመነጨው ንጹህ ኃይል በአለም አቀፍ ደረጃ የአረንጓዴ ልማት መሪ እየሆነች መጥታለች። እነዚህ ስራዎች የኃይል ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ፣ ለአለም የበካይ ጋዞችን የመከላከል ጉዞ የበኩሏን ጉልህ አስተዋፅኦ ያሳየችበት አውድ ነው። በተመሳሳይ መልኩ የሸበሌ ሪዞርት ባህላዊ እሴቶቻችንን ከዘመናዊነት ጋር አቀናጅቶ፣ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ ያላትን ሰፊ አቅም ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የመለወጥ ብቃቷን ያሳየበት የ‘ገበታ ለትውልድ’ ድንቅ ውጤት ነው። በአጠቃላይ ትላንት በሰላም እጦት ይታወቁ የነበሩ አካባቢዎች ዛሬ የልማት ተምሳሌት መሆናቸው፣ ሀገራችን እየገነባች ያለቸው ሰላም ለልማት ማገር መሆኑን ያረጋግጣል። ኢትዮጵያ የምታልም ብቻ ሳትሆን ሕልሟን ወደ እውነት የምትቀይር፣ የቀጠናውን የልማት ተስፋ የምታለመልምና የአፍሪካ ኩራት ሆና የምትቀጥል ቆራጥ ሀገር ናት። ትላንት የተመረቁት ፕሮጀክቶች የነገዋን ብልፅግና የምናረጋግጥባቸው ኩሩ ቅርሶቻችን ናቸው። መንግሥት ከቀጠናው ሀገራት ጋር በመሆን ለጋራ ብልፅግና የሚተጋበትን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል። ህዝባችንም ይህንን የታሪክ እጥፋት በአግባቡ በመረዳትና ለላቀ ሥራ በመነሳሳት የሀገራችንን ከፍታ እንዲያረጋግጥ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ኢትዮጵያ በቀጠናው የብልፅግና ጮራ፣ በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ሆና መዝለቋን ትቀጥላለች! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! የኢፌድሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጥር 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
የሐሳብ የበላይነትን መሠረት ያደረገ ውድድር ለማካሄድ መዘጋጀታቸውን ፓርቲዎች ገለጹ
Feb 1, 2026 73
ወልቂጤ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የሐሳብ የበላይነትን መሠረት ያደረገ ውድድር ለማካሄድ መዘጋጀታቸውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አመራርና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ደምስ ገብሬ፤ መጪው ምርጫ የሐሳብ የበላይነት ጎልቶ የሚወጣበት እንዲሆን እንሠራለን ብለዋል። ፓርቲው በምርጫው የተሻለ ሐሳብ ይዞ በመቅረብና በፖሊሲ አማራጮች ላይ ክርክሮችና ፉክክሮችን በማድረግ የሕዝብ ይሁንታ ለማግኘት በቂ ዝግጅት እያደረገ መሆኑንም ለኢዜአ ተናግረዋል። ለዘላቂ ሰላም፣ ልማትና የሕግ የበላይነት መስፈን በሐሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ አካሄድ መከተል አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ፓርቲው ፍትሐዊ ምርጫ እንዲካሔድ የድርሻውን ከመወጣት ባለፈ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ሥርዓት መጠናከር የሚጠበቅበትን ሚና ይወጣል ብለዋል። የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባልና በብልጽግና ፓርቲ የጉራጌ ዞን ተወካይ ሔኖክ አብዱልሰመድ በበኩላቸው፤ ምርጫው ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። ምርጫው የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል የሚታይበት እንዲሆንም ፓርቲው ያላሰለ ጥረት እንደሚያደርግ አማላክተዋል። ፓርቲያቸው የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ሊቀይሩ በሚችሉ ተጨባጭ ጉዳዮች ላይ በማተኮር እንደሚወዳደር ያስታወቁት ደግሞ በእናት ፓርቲ የጉራጌ ዞን አካባቢ ሰብሳቢ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ፀሐፊ እንዳለ ኤርጌዶ ናቸው። የምርጫ ውድድሩ በፖሊሲ አማራጮችና በሐሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን እየሠሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል። በጋራ ምክር ቤቱ የሚገኙ ሁሉም ፓርቲዎች ለምርጫው ስኬታማነት፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት የበኩላቸውን ለመወጣት እየሠሩ መሆኑም ነው የተገለጸው።
ለምርጫው ሂደት መሳካት የዜጎች ተሳትፎ እንዲጎለብት የሚጠበቅብንን ኃላፊነት እንወጣለን -የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች
Jan 31, 2026 90
ሀዋሳ፤ ጥር 23/2018(ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምርጫው መሳካት የዜጎች ተሳትፎ እንዲጎለብት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት እየሰሩ መሆኑን በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ገለፁ፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ በቁጥር 1113/2011 የመንግሥት አሠራር በግልጽነት፣ በተጠያቂነትና በአሳታፊነት እንዲከናወን ለማድረግ የነቃና በነፃነት የተደራጀ ማኅበረሰብ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን በማመን ሊወጣ ችሏል። በአገሪቱ ልማትና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸው ሚና እንዲጎለብት ለማድረግ እና የተመቻቸ ምህዳር ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን በመረዳትም አዋጁ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ወጥቷል። በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችም ዘንድሮ የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ሠላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ለኢዜአ ገልፀዋል፡፡ የኢየሩሳሌም የሕፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የሀዋሳና አካባቢው ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ማስረሻ ክብረት ምርጫ ዜጎች የመምረጥና የመመረጥ መብታቸውን በተሳትፎ የሚያረጋግጡበት የዴሞክራሲ ባህል መገለጫ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዴሞክራሲ ሊጎለብት የሚችለው ደግሞ የምርጫ ሂደቱ ሠላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ይዘት ሲኖረው እንደሆነ ጠቅሰው ሁላችንም ለዚህ ስኬት የበኩላችንን ጥረት ማድረግ አለብን ብለዋል፡፡ ድርጅታቸው ከእድሮች፣ ከሴቶችና ወጣት ማህበራት ጋር እንደሚሰራ ገልፀው በነዚህ ተቋማት አማካኝነት ህብረተሰቡ በሀገራዊ ምርጫው ንቁ ተሳትፎ እንዲኖረው ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የ“ሻይኒ ዴይ” የማህበረሰብ ልማት አገልግሎት ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጌታቸው ዘውዴ (ዶ/ር) በበኩላቸው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ ሂደት ውስጥ ማህበረሰቡ መብትና ግዴታውን አውቆ በመምረጥም ሆነ በመመረጥ መሳተፍ እንዲችል የግንዛቤ ስራ ይሰራሉ ብለዋል፡፡ ድርጅታቸው ዜጎች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድህረ ምርጫ ወቅት ሊያከናውኗቸው የሚችሉትንና ማከናወን ያለባቸውን ዝርዝር ጉዳዮች የማስገንዘብ ፈቃድ ከምርጫ ቦርድ ማግኘቱንም ጠቁመዋል፡፡ ድርጅታቸው በተለይም ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞችና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎችን ማዕከል አድርጎ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እንደሚሰራ የገለፁት ደግሞ የ“ሴንተር ኦፍ ኮንሰርን” ፕሮግራም ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳንኤል ግዛቸው ናቸው፡፡ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሻለ ግንዛቤ ኖሯቸው በተሻለ መንገድ እንዲሳተፉ በማድረግ የምርጫ ሂደቱ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሰሩ እንደሚገኙ ነው የተናገሩት፡፡
ቦርዱ እያከናወናቸው ያሉ የሕግና የአሠራር ሥርዓት ማሻሻያዎች ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር በኩል ከፍተኛ ድርሻ አላቸው
Jan 30, 2026 134
አዲስ አበባ፤ ጥር 22/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እያከናወናቸው ያሉ የሕግና የአሠራር ሥርዓት ማሻሻያዎች ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ይበልጥ ዴሞክራሲያዊነት ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር በኩል ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ፡፡ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሐሳብ የበላይነት እና በሕዝብ ይሁንታ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲካሄድ የጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱ ይታወሳል። በዚህም የዕጩዎች ምዝገባ ከጥር 1 እስከ የካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሁም የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ይከናወናል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ምርጫው ሰላማዊና ስኬታማ እንዲሆን ምክር ቤቱ ልዩ ዕቅድ አውጥቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ሰፊ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቅሰው፣ ለዚህም በቢሾፍቱ የተደረሰው የሰላም ቃል ኪዳን እንደ ትልቅ ስኬት እንደሚጠቀስ አስረድተዋል። ምርጫው ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን መንግስት እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎችን አድንቀው፣ በተለይም በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀው የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ማሻሻያ አዋጅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የአዋጁ መሻሻል ችግሮችን በንግግር መፍታት እንደሚቻል ያሳየና ለነፃ ምርጫ ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነውም ብለዋል። በተጨማሪም የዘንድሮውን የዕጩዎች ምዝገባ ለየት የሚያደርገው በዲጂታል ዘዴ መከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም የሀገሪቱን የቴክኖሎጂ ጉዞ የሚያግዝ መሆኑን አብራርተዋል። 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሀገሪቱ በብሔራዊ ምክክር እና በፖለቲካዊ መረጋጋት ሂደት ውስጥ ባለችበት ወቅት መከናወኑ ትልቅ ትርጉም አለው ብለዋል። ሰላምና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የማይነጣጠሉ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ሰለሞን፣ ሁሉም ፓርቲዎች ሕግና ሥርዓትን አክብረው መንቀሳቀስ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ለትውልድ የሚተላለፍ ጠንካራ ሀገር እና ነፃ የዴሞክራሲ ባህል መገንባት የሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ኃላፊነት መሆኑንም ነው የተናገሩት። ምክር ቤቱ ምርጫው ፍፁም ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ከመንግስት ጋር በቅንጅት መስራቱን እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በክልሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተሰጡ አቅጣጫዎች መሰረት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ፍጥነትና ፈጠራን መሰረት ባደረገ መልኩ ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jan 30, 2026 141
አዲስ አበባ፤ ጥር 22/2018(ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተሰጡ አቅጣጫዎች መሰረት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ፍጥነትና ፈጠራን መሰረት ባደረገ መልኩ እናስቀጥላለን ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ። በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች በመደመር መንግሥት እይታ የዘርፎች እመርታ ሥልጠና ማጠቃለያ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተሰጡ አቅጣጫዎች ግቦች አፈፃፀም ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱም አቶ ጌቱ ወዬሳ እንዳሉት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተሰጡ አቅጣጫዎች መሰረት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት በውጤታማነት እንዲቀጥሉ አመራሩ በቁርጠኝነት ይሰራል። በክልሉ በተለይም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ፤ የቅዳሜ እና የእሁድ ገበያን በማስፋፋት አምራችና ሸማችን በማገናኘት እንዲሁም የቁጥጥርና ክትትል ስራዎች በማጠናከር የኑሮ ውድነት ለመቀነስ እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል። የዲጂታላይዜሽን አሰራሮችን በማሳደግ እንዲሁም ተጠያቂነትን በማስፈን፤ የሰላም እሴት ግንባታ ስራዎች የማሳደግ እንዲሁም ጠባቂነትን ለመቀነስ እየተደረጉ የሚገኙ ርብርቦችን አጠናክረን እናስቀጥላለን ነው ያሉት። ለአርሶ አደሩ ተገቢውን ድጋፍ በማድረግ በክልሉ የሚታረስ መሬት ፆሙን እንዳያድር የማድረግ፤ በምግብ ራስን ለመቻልና ከተረጂነት ለመላቀቅ እንዲሁም ኮንትሮባንድንና የመሬት ወረራንና ህገወጥ ግንባታን ዜሮ ለማድረግ የሚሰሩ ስራዎች የበለጠ ይጠናከራሉ ብለዋል። የገጠር ኮሪደር፣ የምርት ማከማቻ ግንባታን የማፋጠን፣ የሽያጭ ማዕከልና አግሮ ፕሮሰሲንግ ግንባታ እንዲሁም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማስፋት እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ፍጥነትና ፈጠራ በታከለበት መልኩ እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። የሌማት ትሩፋትን በማስፋት፣ የበጋ እርሻና የኩታ ገጠም ስራዎችን የማሳደግ እንዲሁም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማሳደግ፤ ለኢንቨስትመንት ዘርፉ ተገቢው ድጋፍ በማድረግ እንዲጎለብት ማስቻል፤ የማዕድን ዘርፉ ላይ ያሉ ሀብቶችን ለመጠቀም የሚሰሩ ስራዎች እንዲሁ ይጠናከራሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን በማጠናከር ኢንዱስትሪዎችን የማሳደግ ስራ ላይም እየተሰሩ የሚገኙ ጅምር ስራዎችን ለማሳደግም ትኩረት ተደርጓል ብለዋል። የተቀመጡ አቅጣጫዎች ተግባራዊ ስለመሆናቸው የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰራም ነው አቶ ጌቱ ያስገነዘቡት።
ማህበራዊ
ለአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የጤና አገልግሎትን ተደራሽነት ለማሳካት ለጤና መድህን አገልግሎት ትኩረት ተሰጥቷል
Feb 1, 2026 90
ሰመራ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የጤና አገልግሎትን ተደራሽነትና ጥራት ለማሳካት ለጤና መድህን አገልግሎት ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ። በኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት የአፋር ክልል ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀምና የቀጣይ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መሐመድ ሁሴን እንደተናገሩት፤ በክልሉ የህብረተሰብ ጤና አገልግሎትን ተደራሽነትና ጥራት ለማሳካት ለጤና መድህን አገልግሎት ትኩረት ተሰጥቷል። ለዚህም በክልሉ ባሉ ሁሉም ወረዳዎች አገልግሎቱን ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊው እገዛ እንደሚደረግ ጠቁመዋል። የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኀላፊ አቶ ዊቲካ ኖሬ በበኩላቸው፤ የክልሉን ማህበረሰብ የጤና አገልግሎት ጥራትና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በቅንጅት መሰራቱን አንስተዋል። ተግባሩን በማጠናከር የጤና አገልግሎቱን ውጤታማ ለማድረግ አሰራሩን የማዘመንና የጤና መድህን አገልግሎትን ለማስፋፋት መሰራቱን ተናግረዋል። በዚህም በክልል ደረጃ የተጠቃሚ አባዎራዎችና እማዎራዎችን ቁጥር ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የአመራሩን ቁርጠኝነት እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ያምሮት አንዷለም እንዳሉት፤ እንደ ሀገር የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎትን ፍትሃዊነትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው። በአፋር ክልልም አገልግሎቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ መረጃዎች በአንድ ቋት ውስጥ የማካተት ስራ መከናወኑን ጠቁመዋል። በክልሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ያልሆኑ ወረዳዎችን ወደ ስራው ለማካተት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። በመድረኩ የአፋር ክልል ከፍተኛ የስራ ኀላፊዎችና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።
መንግስት ለባህላዊ ፍርድ ቤቶች የሰጠው ህጋዊ እውቅና ለፍትህ ስርዓቱ ተደራሽነት ተጨማሪ አቅም ፈጥሯል
Feb 1, 2026 127
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ መንግስት ለባህላዊ ፍርድ ቤቶች የሰጠው ህጋዊ እውቅና ለፍትህ ስርዓቱ ተደራሽነት ተጨማሪ አቅም መፍጠሩን የፍትሕ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ታሪክ ውስጥ ሽምግልና፣ የገዳ ሥርዓት፣ አበጋርና ሌሎችም ባህላዊ የግጭት መፍቻ ሥርዓቶች እንደ ማህበረሰቡ ዋና እሴቶች ሆነው ዘልቀዋል፡፡ ይሁን እንጂ መንግስታት ሲለዋወጡ ዘመናዊ የሕግ ሥርዓትን ለመከተል በሚያደርጉት ጥረት፣ ለባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች የሚሰጣቸው ትኩረትና ተቀባይነት እየቀነሰ ቆይቷል፡፡ በፍትሕ ሚኒስቴር የፍትሕ ሥርዓት ማሻሻያ ዳይሬክተር ኖህ ታከለ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠሩ ግጭቶችን ዘላቂ ግንኙነትን በሚያጠናክር መንገድ የሚፈቱባቸው ሥርዓቶች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ባህላዊ የግጭት መፍቻ ሥርዓቶች ለዘመናት ማህበረሰቡን በሰላምና በአብሮነት አጽንተው የቆዩ ጥንታዊ እሴቶች ቢሆኑም፣ አሁን ላይ መንግሥት ሕጋዊ ዕውቅና መስጠቱ ለፍትሕ ሥርዓቱ ተደራሽነትና ጥራት አዲስ አቅም መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ በርካታ ዜጎች በባህላዊ የግጭት አፈታት ስልቶች በሚሰጡ ውሳኔዎች ደስተኛ መሆናቸው በጥናት ተለይቷል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ይህም ማህበረሰቡ ለባህሉና ለእሴቱ የላቀ ቦታ እንደሚሰጥ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በተከናወኑ የፍትሕ ዘርፍ ሪፎርሞች እነዚህ እሴቶች ለሰላምና መረጋጋት ያላቸውን አበርክቶ ታሳቢ በማድረግ፣ በቂ ትኩረት ተሰጥቷቸው የትግበራ ሕግ እንዲወጣላቸው ተደርጓል ብለዋል፡፡ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች የመንግሥትንና የዜጎችን ወጪ የሚቀንሱ በመሆናቸው፤ በአሁኑ ወቅት ወደ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች የሚሄዱ ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተናግረዋል፡፡ የፍትሕ ሚኒስቴር ክልሎች የራሳቸውን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ሕግ እንዲያወጡ ሞዴል ሕግ ማዘጋጀቱን በመጥቀስ፤ ስምንት ክልሎች እስካሁን ተግባራዊ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡ ክልሎቹ ያወጧቸው ሕጎች ከሕገ-መንግሥቱ ጋር የሚጣጣሙ መሆናቸውንና የዜጎችን ፍላጎት ማርካታቸውን በጥናት በመለየት ለባህላዊ የግጭት አፈታት ስልቶች ዕውቅና እንደሚሰጡ አስረድተዋል፡፡ በአንዳንድ ክልሎች ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ከመደበኛው ፍርድ ቤት ጋር ተቀራራቢ የሆኑ የክስ መዝገቦችን እየተመለከቱ መሆኑን በማንሳት፤ ለአብነት በኦሮሚያ ክልል ከ7 ሺህ በላይ ቀበሌዎች የባህላዊ ፍርድ ቤት መዝገብ ማደራጀታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በመጀመሪያና በይግባኝ ደረጃ በተቋቋሙ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች የተላለፉ ውሳኔዎች በፈቃደኝነት የማይፈጸሙ ከሆነ፣ መደበኛው ፍርድ ቤት ውሳኔዎቹን የማስፈጸም ግዴታና መብት ተሰጥቶታል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሲቪልና ፖለቲካ መብቶች ዘርፍ ኮሚሽነር አብዲ ጅብሪል (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች መቋቋም የፍትሕ ተደራሽነትን በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል፡፡ ሰብዓዊ መብቶችን ለማክበርና ለማስከበር የፍትሕ ተደራሽነት ቀዳሚ ተግባር መሆኑን በመጥቀስ፤ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ሰብዓዊ መብቶችን ለማስተማርና ግንዛቤ ለመፍጠር ወሳኝ መድረክ እንደሚሆኑም አብራርተዋል፡፡ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች በማህበረሰቡ ዘንድ ሰፊ ተቀባይነት ያላቸው በመሆናቸው፣ ተገቢው ዕውቅና ተሰጥቷቸው በሕግ ማዕቀፍ እንዲቋቋሙ መደረጉ ተገቢ መሆኑን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል፡፡
ቴክኖሎጂን በመጠቀም የዜጎችን የፍትሕ አገልግሎት ቀልጣፋ ማድረግ ተችሏል
Feb 1, 2026 57
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- ቴክኖሎጂን በመጠቀምና የጉዳዮች ፍሰት መመሪያን በመተግበር የዜጎችን የፍትሕ አገልግሎት ቀልጣፋ ማድረግ መቻሉን የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሌሊሴ ደሳለኝ ገለጹ፡፡ የፍትሕ ሥርዓቱን በማሻሻል ሕብረተሰቡ የሚያገኘውን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግ ሰፊ የሪፎርም ሥራ መከናወኑን አውስተዋል። በዚህም መሠረት ባህላዊ የግጭት አፈታት ስልቶች አማራጭ የሙግት መፍቻ ሥርዓቶች በመሆን የሕግ ድጋፍና ዕውቅና እንዲኖራቸው ተደርጓል ነው ያሉት። በኢትዮጵያ የፍርድ ቤት አስማሚነትን ተግባራዊ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱ እንዲሻሻል መደረጉንም አስታውቀዋል። በፌደራልና በክልል ፍርድ ቤቶች በርካታ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን ጠቅሰው፤ በፍርድ ቤት አስማሚነት ከፍተኛ የክርክር መጠን ያላቸው ጉዳዮች በስምምነት እንዲፈቱ መደረጉን አረጋግጠዋል። የፍርድ ቤቶች የሪፎርም ሥራዎች የማኅበረሰቡን የተፋጠነ ፍትሕ ፍላጎት እንዲሻሻል ማስቻላቸውንም አመላክተዋል። በክርክር አመራርና የውሳኔ ጥራት ላይ ቅሬታዎች ሲነሱ እንደነበር አውስተው፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ባለጉዳዮች ጥራት ያለው አቤቱታና መረጃ እንዲያቀርቡ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። የሰበር ችሎት ውሳኔዎች በሠነድ ተደራጅተው እንዲቀመጡ በማድረግ ለዐቅም ግንባታና ለውሳኔዎች ተመሳሳይነት ከፍተኛ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ባለፈም ቴክኖሎጂን በመጠቀም ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልጸው፤ የጉዳዮች ፍሰት መመሪያ ተግባራዊ መደረጉ ለሥራው ተጨማሪ ዐቅም እየፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል።
ሀገራዊ ምክክሩ ልማቷ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስረከብ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው
Feb 1, 2026 54
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ምክክሩ ሰላምና ልማቷ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን የሸገር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ አቶ ከበደ ኩምሳ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ ምክክሩ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት ትልቅ በር የከፈተ መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም ችግሮችን በምክክር በመፍታት ሀገርን በጋራ የመገንባት ሂደት እውን እንዲሆን ምክክሩ የጎላ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፤ ለስኬቱም የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በተጨማሪም የቆዩ ችግሮችን በምክክር በመፍታት ዘላቂ ሠላምና አብሮነትን ይበልጥ ለማጠናከር ሁነኛ መፍትሔ መሆኑን ጠቁመው፤ ለነገዋ የበለፀገች ኢትዮጵያ መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ጫሊ ወርቅነህ በበኩላቸው፤ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ምክክሩ ችግሮችን በመፍታት በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ የሚያስችል ነው ያሉት አስተያየት ሰጭዋ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ለዘላቂ ልማትና ለሕዝቦች አብሮነት ጠንካራ መሠረት የሚጥል መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቱ አለመግባባቶችን በምክክር በመፍታት በጋራ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ብሔራዊ መግባባት ለማጎልበት እየሠራ መሆኑ ይታወቃል። ሀገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ፣ ጠንካራ ሀገረ መንግሥትን ለመገንባት እና የዴሞክራሲ ባህልን ለማዳበር ትልቅ ዕድል የሚሰጥ መሆኑም ይታመናል።
ኢኮኖሚ
የሀገር ውስጥ ገበያውን ለማረጋጋት የሚጥሩ ፋብሪካዎች ሀገራዊ አበርክቷቸው ቀላል አይደለም-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Feb 1, 2026 43
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ የሀገር ውስጥ ገበያውን ለማረጋጋት የሚጥሩ ፋብሪካዎች ሀገራዊ አበርክቷቸው ቀላል የሚባል አይደለም ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አስገነዘቡ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ የሚገኘውን አማጋ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካን መጎብኘታቸውን ገልጸዋል። በቅርቡ ወደ ሥራ የገባው ፋብሪካው፤ ተከላው ሙሉ በሙሉ በቅርቡ ሲጠናቀቅ በዋናነት ብርድ ልብስ፣ የአልጋ ልብስ፣ የሶፋ ልብስ፣ መጋረጃ፣ የአንሶላ ጨርቅ፣ ጂንስ እና ሁሉንም አይነት የጨርቃ ጨርቅ ምርቶች በተለየዩ ዲዛይኖች እና ልኬት ማምረት ያስችለዋል ብለዋል። ጥራት ያላቸው ተኪ ምርቶችን የሚያመርቱና በቀጥታ ምርቶችን ለውጭ ገበያ ከማቅረብ ይልቅ፤ የሀገር ውስጥ ገበያውን ለማረጋጋት የሚጥሩ ፋብሪካዎች ሀገራዊ አበርክቷቸው ቀላል የሚባል አይደለም ሲሉም አስገንዝበዋል።
የግብርና ምርታማነትንና የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተቀየሱ ስትራቴጂዎች እየተተገበሩ ነው
Feb 1, 2026 131
አዳማ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- የግብርናን ምርታማነትና የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተቀየሱ ስትራቴጂዎች እየተገበሩ መሆኑን የተለያዩ ክልሎች የግብርና ቢሮ አመራሮች አስታወቁ። የግብርና ሜካናይዜሽን እና የከተማ ግብርና ስትራቴጂዎች፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ የገቢ ምርቶችን ለመተካት እና የወጪ ንግድን ለማሳደግ የጎላ ሚና እንዳላቸው ይታመናል። በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር እንዳሉት፤ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታውን ለማሳደግ የግብርና ሜካናይዜሽን እና የከተማ ግብርና ጉልህ ድርሻ አላቸው። ቀደም ሲል ሲሠራ የነበረውን የግብርና ሜካናይዜሽን እና የከተማ ግብርናን በተደራጀ አግባብ ለማስፈጸም የተዘጋጁ ስትራቴጂዎች ተጨማሪ ዐቅም እንደሆኑም አንስተዋል። የከተማ ግብርና ስትራቴጂው ከተሞች ሸማች ብቻ ሳይሆኑ አምራች እንዲሆኑና የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ የሚደረገውን ግብ ለማሳካት አበርክቶው የጎላ መሆኑንም ለኢዜአ ተናግረዋል። የከተማ ግብርና ከኢኮኖሚው ባሻገር የሥነ-ምኅዳር ሚዛንን ለመጠበቅ፣ የሥራ ባህል ለማሻሻል እና የሀብት ምንጭ በመሆንም በርካታ ፋይዳ እያስገኘ መሆኑን አስረድተዋል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሶ ፈይሳ በበኩላቸው፤ የከተማና የገጠር ግብርና ልማትን ለማሳደግ ሁሉንም አካል ያሳተፈ እንቅስቃሴ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል። በተለይም የዘርፉን የአሠራር ሥርዓት አካታችና አሳታፊ በማድረግ የዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ የሚወጡ ስትራቴጂዎችን በዕቅድ በማስደገፍ ለተግባራዊነቱ በክልሉ እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል። በክልሉ ሜካናይዜሽንን ለማስፋት በየደረጃው በተደረገው ጥረት አሁን ላይ 50 በመቶ የሚሆነው የእርሻ መሬት በሜካናይዜሽን ታግዞ እየለማ መሆኑንም ለአብነት አንስተዋል። ይህም ምርታማነትን ለማሳደግና የምርት ብክነትን በማስቀረት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ አስችሏል ብለዋል። በቀጣይም ለግብርና ሜካናይዜሽን እና ለከተማ ግብርና ስትራቴጂ ተፈጻሚነት አበክረን በመሥራት የዘርፉን ምርታማነት እናረጋግጣለን ነው ያሉት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከዩናይትድ ኪንግደም የኮመንዌልዝ፣ ልማት ጉዳዮች እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይቬት ኩፐር ጋር ተወያዩ
Feb 1, 2026 76
አዲስ አበባ፣ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዩናይትድ ኪንግደም የኮመንዌልዝ፣ ልማት ጉዳዮች እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይቬት ኩፐርን ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ የዩናይትድ ኪንግደም የኮመንዌልዝ፣ ልማት ጉዳዮች እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይቬት ኩፐርን አግኝቼ በቁልፍ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል ብለዋል። ከውይይታቸው ጎን ለጎን በተካሄደው የኢንቨስትመንት አማካሪዎች ማእቀፍ ሥር የኢንቨስትመንት እና ኃብት አስተዳደር የቴክኒካል ትብብር የመግባቢያ ሥምምነት እና የሁለት የጋራ የልማት ስምምነቶች ፊርማ መርሃ ግብር ላይም ተገኝተናል ነው ያሉት። እነዚህም የሁርሶ-አይሻ 400 ኪሎ ቮልት እና የደገሃቡር-ቀብሪደሃር 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክቶች ስምምነቶች ናቸው ብለዋል። እነዚህ ስምምነቶች ትብብርን በማጠናከር እና ስትራቴጂያዊ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት ረገድ ትልቅ ርምጃን የሚያሳዩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ለሕብረቱ የመሪዎች ጉባዔ ለሚመጡ እንግዶች አፍሪካዊ ባህልን የሚያንጸባርቁ አልባሳትና ጌጣጌጦች አዘጋጅተናል- ነጋዴዎች
Feb 1, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- ለ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ለሚመጡ እንግዶች አፍሪካዊነትን የሚያንጸባርቁ የባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች ማዘጋጀታቸውን የሀገር ባህል አልባሳት ጌጣጌጥ ነጋዴዎች ገለጹ። በባህል አልባሳት ንግድ የተሰማሩት ይላቅ በሺወርቅ፤ በአዲስ አበባ የሚከናወኑ መድረኮች መበራከት የባህል አልባሳትን ለማስተዋወቅና ገቢ ከማግኘት አንጻር ሰፊ ዕድል መፍጠራቸውን አንስተዋል። ለአፍሪካ ሕብረት ጉባዔ ለሚመጡ እንግዶችም ጥራት ያላቸው የባህል አልባሳት ማዘጋጀታቸውን ለኢዜአ ገልጸዋል። ምስጢረ ነጋሽ በበኩላቸው አፍሪካዊ አንድነትን የሚገልጹ ቀለማትና ምልክቶች የታተሙባቸው አልባሳት ማዘጋጀታቸውን ገልጸው፤ ይህም እንግዶች የሀገራቸውን ያህል እንዲሰማቸው ለማድረግ ይረዳል ብለዋል። ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ እንግዶች የባህል ምርቶችን የመጎብኘትና የመግዛት ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ ነጋዴ ማርታ መንግሥቱ ናቸው። ለሕብረቱ ጉባዔ የሚመጡ እንግዶችን በታማኝነት በማስተናገድ የሀገራችንን ገጽታ ከመገንባት ጎን ለጎን ምርቶቻችንን ለማስተዋወቅ ተዘጋጅተናል ብለዋል። በባህል ጌጣጌጦችና አልባሳት ንግድ የተሰማሩት ሳራ ብርሃኑ እና ፍሬው ለማ በበኩላቸው፤ የኢትየጵያን ብዝኃ-ባህል የሚወክሉ አልባሳት፣ ቅርፃቅርፆችና ሥዕሎችን አዘጋጅተው እንግዶችን በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። ይህ አጋጣሚ የሀገርን ገጽታ ለመገንባት፣ የኢትዮጵያን ባህልና ዕሴት ለዓለም ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ቴክኖሎጂን በመጠቀም የዜጎችን የፍትሕ አገልግሎት ቀልጣፋ ማድረግ ተችሏል
Feb 1, 2026 57
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- ቴክኖሎጂን በመጠቀምና የጉዳዮች ፍሰት መመሪያን በመተግበር የዜጎችን የፍትሕ አገልግሎት ቀልጣፋ ማድረግ መቻሉን የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሌሊሴ ደሳለኝ ገለጹ፡፡ የፍትሕ ሥርዓቱን በማሻሻል ሕብረተሰቡ የሚያገኘውን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግ ሰፊ የሪፎርም ሥራ መከናወኑን አውስተዋል። በዚህም መሠረት ባህላዊ የግጭት አፈታት ስልቶች አማራጭ የሙግት መፍቻ ሥርዓቶች በመሆን የሕግ ድጋፍና ዕውቅና እንዲኖራቸው ተደርጓል ነው ያሉት። በኢትዮጵያ የፍርድ ቤት አስማሚነትን ተግባራዊ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱ እንዲሻሻል መደረጉንም አስታውቀዋል። በፌደራልና በክልል ፍርድ ቤቶች በርካታ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን ጠቅሰው፤ በፍርድ ቤት አስማሚነት ከፍተኛ የክርክር መጠን ያላቸው ጉዳዮች በስምምነት እንዲፈቱ መደረጉን አረጋግጠዋል። የፍርድ ቤቶች የሪፎርም ሥራዎች የማኅበረሰቡን የተፋጠነ ፍትሕ ፍላጎት እንዲሻሻል ማስቻላቸውንም አመላክተዋል። በክርክር አመራርና የውሳኔ ጥራት ላይ ቅሬታዎች ሲነሱ እንደነበር አውስተው፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ባለጉዳዮች ጥራት ያለው አቤቱታና መረጃ እንዲያቀርቡ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። የሰበር ችሎት ውሳኔዎች በሠነድ ተደራጅተው እንዲቀመጡ በማድረግ ለዐቅም ግንባታና ለውሳኔዎች ተመሳሳይነት ከፍተኛ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ባለፈም ቴክኖሎጂን በመጠቀም ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልጸው፤ የጉዳዮች ፍሰት መመሪያ ተግባራዊ መደረጉ ለሥራው ተጨማሪ ዐቅም እየፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል።
የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ዲጂታል ክህሎታችንን በማጎልበት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታችንን እያሳደገልን ነው
Jan 31, 2026 73
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018(ኢዜአ)፦ የአምስት ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ዲጂታል ክህሎትን በማጎልበት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን እያሳደገላቸው መሆኑን ወጣቶች ገለጹ። በወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት ባለፉት ስድስት ወራት ከ62 ሺህ በላይ ወጣቶች የሥራ ዕድል የሚፈጥሩበትን የኢትዮ-ኮደርስ ዲጂታል ክህሎት ስልጠና ማጠናቀቃቸውን የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሐምሌ 16/2016 ዓ.ም ያስጀመሩት የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ እና በኢትዮጵያ መንግስታት የሚተገበር መርሃ ግብር ነው። በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዌብ ፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስና በሰው ሰራሽ አስተውሎት መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት ላይ 5-ሚሊዮን ወጣቶች በኦንላይን የኮዲንግ ስልጠና እንዲወስዱ ተመቻችቷል። የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮም በ5-ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠናን ያጠናቀቁ ወጣቶች የዕውቅና መርሃ ግብር አካሂዷል። የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ካጠናቀቁ ወጣቶች መካከል የአብስራ መርሃፅድቅ፤ ስልጠናው ዘመኑ የሚጠይቀውን የዲጂታል ክህሎት ማበልጸግ የሚያስችል ወሳኝ ዕድል ነው ብላለች። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወጣት አብርሃም ይልቃል በበኩሉ፤ ስልጠናው የዲጂታል ክህሎትን ለማሻሻል የተመቻቸ ዕድል በመሆኑ ሁሉም ወጣት ሊጠቀምበት እንደሚገባ ገልጿል። ወጣት ታዱ ክፍሌ፤ በበኩሉ የ5 ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን በማሻሻል ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን በማሳደግ ሥራ የሚፈጥሩበትን አቅም እንደፈጠረላቸው ገልጿል። የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ዲጂታል ክህሎታችንን በማጎልበት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታችን እያሳደገልን ነው ያለው ደግሞ ወጣት ታሪኩ አዱኛ ነው። የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ክብርዓለም ደምሴ በበኩላቸው፤ ባለፉት ስድስት ወራት በወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት ከ62 ሺህ በላይ ወጣቶች የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ማጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ መነሻነት የስብዕና መገንቢያ ማዕከላትን ወጣቶች የሥራ ዕድል የሚፈጥሩበትን የቴክኖሎጂ ክህሎት አቅም እንዲገነቡ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
የፋይዳ መታወቂያ አካታች በመሆኑ የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው
Jan 31, 2026 108
ሰመራ፤ ጥር 23/2018(ኢዜአ)፦ የፋይዳ መታወቂያ አካታች በመሆኑ የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የንቅናቄ መርሃ ግብር በሰመራ ከተማ ተካሂዷል። በንቅናቄ መድረኩ የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ከይረዲን ፋይዳ መታወቂያ አካታች በመሆኑ የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል። በተያዘው ዓመት 30 ሚሊየን ሴቶችና 10 ሚሊየን ህፃናት የመታወቂያው ባለቤት ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አንስተው ዕቅዱን ለማሳካት በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት። የፋይዳ መታወቂያ አካታችነት ሴቶች ተጠቃሚ የሚሆኑበት፣ መብቶቻቸውን ማረጋገጥ የሚችሉበትና የሴቶችና ህፃናትን ክብርና ጥቅም ማሳደግ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል። በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ መሐመድ ሁሴን በበኩላቸው የፋይዳ መታወቂያ የሴቶችን መብት ከማስጠበቅ አኳያ ከፍተኛ ፋይዳ አለው ብለዋል። ሴቶች እንደ ሀገር ያላቸው ሁለንተናዊ ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው የፋይዳ መታወቂያም ይህንኑ ተሳትፏቸውን በማጎልበት ተጠቃሚነታቸውን ዕውን ለማድረግ አይነተኛ መሳሪያ መሆኑን ተናግረዋል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ምክትል ዋና ዳይሬክተር ራሄል አብርሃም እንደገለጹት የፋይዳ መታወቂያ ስርዓት መዘርጋት ዜጎች በፍትሃዊነት እንዲገለገሉ መደላድል ፈጥሯል። ዘንድሮ የዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት ከ100 በላይ በሚሆኑ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት 90 ሚሊየን የሚሆኑ ተጠቃሚዎችን ለመመዝገብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ዩኒቨርስቲው ችግር ፈቺ ምርምሮችን ወደ ተግባር ለመቀየር ከባለድርሻ አካላት ጋር ይሰራል
Jan 30, 2026 86
ደሴ ኢዜአ ጥር 22/2018-የወሎ ዩኒቨርሲቲ ችግር ፈቺ ምርምሮችን ወደ ተግባር ለመቀየር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን ገለጸ። ዩኒቨርሲቲው "ተግባራዊ ምርምር ለዘላቂ ሀገራዊ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ 12ኛውን ዓመታዊ የምርምር ኮንፈረንስ በደሴ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል። የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) ዩኒቨርስቲው ከመማር ማስተማር ሥራው ጎን ለጎን የሕብረተሰቡን ችግር የሚፈቱ ምርምሮችን እያካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶች ወደ ተግባር እንዲቀየሩ በየደረጃው ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል። ዩኒቨርስቲው በጤና በትምህርት፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በቴክኖሎጂ፣ በባህልና ኪነጥበብ፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በቴክኖሎጂና በሌሎችም ዘርፎች ያካሄዳቸው የምርምር ውጤቶች ወደ ተግባር ተቀይረው ተጨባጭ ውጤት እንዲያመጡ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል። ለውጤታማነቱም ከፌዴራል፣ ከክልል፣ ከዞንና ከከተማ አስተዳደር ተቋማትና አስፈጻሚ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። በዩኒቨርስቲው ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጢጣ ልዕለ ህክምና ካምፓስ ሕብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት መምህርና ተመራማሪ ጌታው ዋለ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ለተግባራዊ ምርምር በተሰጠ ትኩረት የህብረተሰቡን ችግር ማቃለል መቻሉን አንስተዋል። የሴቶችን፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ እንዲሁም የእናቶች ጤና ክብካቤ ማሳደግ ላይ ያተኮረ ጥናት ማካሄዳቸውንም አመልክተዋል። ይህም ጥናት ወደ ተግባር ለመቀየር ከጊዜ ሰሌዳ ጀምሮ እቅድና መመሪያ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።
ስፖርት
በተጠባቂው ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ከቶተንሃም ሆትስፐርስ ጋር አቻ ተለያየ
Feb 1, 2026 54
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐ-ግብር ቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ማንችስተር ሲቲ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን በማሸነፍ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ ማምሻውን በቶተንሃም ሆትስፐርስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ራያን ቸርኪ በ11ኛው እና አንቶዋን ሴሜንዮ በ44ኛው ደቂቃ ባስቆጠሯቸው ግቦች ማንችስተር ሲቲ 2 ለ 0 መምራት ችሎ ነበር። ከእረፍት መልስ ዶምኒክ ሶላንኬ በ53ኛው እና በ71ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋቸው ግቦች ቶተንሃምን አቻ አድርጓል። በመጀመሪያው አጋማሽ ማንችስተር ሲቲ፣ በሁለተኛው አጋማሽ ቶተንሃም ሆትስፐርስ የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገዋል። የ2 ለ 0 መሪነቱን ማስጠበቅ ያልቻለው ማንችስተር ሲቲ በ47 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ጥሏል። ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ከአራት ወደ ስድስት ከፍ ብሏል። ቶተንሃም ሆትስፐርስ በ29 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ የዛሬውን ጨምሮ ባለፉት ስድስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ዛሬ በተደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን 3 ለ 2 ሲያሸንፍ ብሬንትፎርድ አስቶንቪላን 1 ለ 0 ረቷል። ኖቲንግሃም ፎረስት እና ክሪስታል ፓላስ አንድ አቻ ተለያይተዋል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ነገ ሰንደርላንድ እና በርንሌይ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል።
ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሶስተኛ ከፍ አደረገ
Feb 1, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ18ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ከቤ ብዙነህ በጨዋታ እና ዳዊት ተፈራ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ ተከታታይ ድሉን ያስመዘገበው ነገሌ አርሲ በ32 ነጥብ ደረጃውን ከአራተኛ ወደ ሶስተኛ ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ዘጠነኛ ድሉን አስመዝግቧል። በአንጻሩ በሊጉ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ20 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ተጠባቂ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 አሸንፏል። የቅዱስ ጊዮርጊሱ ቶሎሳ ንጉሴ በ82ኛው ደቂቃ በራሱ ላይ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በውድድር ዓመቱ ስምንተኛ ድሉን ያስመዘገበው ፋሲል ከነማ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ32 ነጥብ ከነበረበት አምስተኛ ደረጃ ወደ አራተኛ ከፍ ብሏል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ለሰባተኛ ጊዜ የተሸነፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ23 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዟል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት ሶስት ተከታታይ ጨዋታዎች አላሸነፈም። በሌላኛው መርሐ-ግብር መቀሌ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። የኢትዮጵያ ቡናው በፍቃዱ አለማየሁ በራሱ ላይ ለመቀሌ 70 እንደርታ፣ አምበሉ ራምኬል ጀምስ ለኢትዮጵያ ቡና ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። መቀሌ 70 እንደርታ በ18 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ኢትዮጵያ ቡና በ20 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ቀን ላይ በተደረገ የመጀመሪያ ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 በመርታት በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 18ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ19ኛ ሳምንት እና የሊጉ የመጀመሪያ ዙር የማጠናቀቂያ መርሐ-ግብር ከጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳል።
ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን በማሸነፍ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ
Feb 1, 2026 57
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በ24ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ዩናይትድ ፉልሃምን 3 ለ 2 በመርታት ደረጃውን ከነበረበት ወደ አራተኛ ከፍ ያደረገ ሲሆን ሶስተኛ ተከታታይ ድሉንም አስመዝግቧል። የማንችስትር ዩናይትድን ግቦች ካስሚሮ በ19ኛው፣ ኩና በ56ኛው እንዲሁም ሴስኮ በ94ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፈዋል። በአንጻሩ ሂምኔዝ በ85ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት እና ኬቪን በ92ኛው ደቂቃ በጨዋታ ለፉልሃም ግቦችን አስቆጥረዋል። ውጤቱን ተከትሎም ማንችስተር ዩናይትድ በ41 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ዳግም የተረከበ ሲሆን፤ ፉልሃም በ34 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሌላ የጨዋታ መርሐ-ግብር ብሬንትፎርድ አስቶንቪላን በሜዳው 1 ለ 0 ሲያሸንፍ፤ ኖቲንግሃም ከክሪስታል ፓላስ አንድ አቻ ተለያይተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
Feb 1, 2026 50
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በ18ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 ረትቷል። 10 ሠዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ፤ ፋሲል ከነማ የቅዱስ ጊዮርጊሱ ቶሎሳ ንጉሴ በራስ ላይ ባስቆጠራት ግብ አሸናፊ ሆኗል። ቀደም ብሎ 9 ሠዓት ላይ በተካሄደው የዕለቱ መርሐ-ግብር መቀሌ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ ቡና አንድ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ አርብቶ አደሩን በማሳተፍ ከ33 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው
Jan 31, 2026 112
ጂንካ፤ ጥር 23/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሩን በማሳተፍ ከ33 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የአፈርና ውሃ ጥበቃና የግጦሽ ሳር መከለል ስራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ኃላፊ ምንላርገው አዲሱ፣ በዞኑ በተጀመረው የተፋሰስ ንቅናቄ ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት 50 ንዑስ ተፋሰሶች የማልማት ስራ እንዲሁም በአርብቶ አደርና በዝቅተኛ አካባቢዎች ደግሞ ከ17 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የግጦሽ ሳር መከለል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ በዞኑ ከ33 ሺህ ሄክታር መሬት የተፋሰስና የግጦሽ ሳር መከለል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፥ የተፋሰስ ልማቱ በተከናወነባቸው ስፍራዎች ከ11 ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተከላ ይከናወናል ነው ያሉት። በዘንድሮው ዓመት የተፋሰስ ልማት በሳይንሳዊ ጥናት የተደገፈ ስነ-አካላዊና ስነ-ህይወታዊ ስራዎች እንደሚከናወኑም ጠቁመዋል። ልማቱ የተከናወነባቸው አካባቢዎችን ከሰውና ከእንሰሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራም ገልጸዋል። በዞኑ ሐመር ወረዳ እየተከናወነ ባለው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የተሳተፉት ወይዘሮ አልጎ በሌ፥ በአካባቢው የቡስካ ጥብቅ ደን እንደሚገኝ ተናግረዋል። ቀደም ሲል ደኑ በሰውና በእንስሳት ጉዳት ይደርስበት እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ ደኑን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ የመጠበቅ ስራ ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። በአካባቢያችን የተፋሰስ ልማት ከተጀመረ ወዲህ አካባቢው ለእርሻ ተስማሚ መሆን ጀምሯል ያሉት አቶ አስ ኦቶሎ ለእንስሳት የሚሆን በቂ የግጦሽ ሳር የምናገኝበት ዕድልንም እየፈጠረ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ለመስጠት ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች ነው
Jan 29, 2026 123
አርባምንጭ፤ ጥር 21/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ዓለምአቀፍ ተግዳሮት ለሆነው አየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ለመስጠት ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች መሆኗን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስገነዘበ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአካባቢ አየር ንብረት ለውጥ ዘርፍና የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ነው። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴዔታ ስዩም መኮንን በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እንዲሁም የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ላይ በትኩረት እየሠራች ነው ብለዋል። ዓለምአቀፍ ተግዳሮት ለሆነው የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ለመስጠትም ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች መሆኗን አስገንዝበዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብርን ጨምሮ በሀገር በቀል ስልቶች ለአየር ንብረት ለውጥ እየተሰጠ ባለው ምላሽም ተጨባጭ ውጤት መምጣቱን አረጋግጠዋል። የኢፌዴሪ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ እንዳሉት፤ ዜጎች ንጹህና ጤናማ በሆነ አካባቢ የመኖር መብታቸውን ለማረጋገጥ የጽዱና አረንጓዴ ልማት ሥራዎች ተሠርተዋል። የከተሞች ኮሪደር ልማትን ጨምሮ የጽዱ ኢትዮጵያ፣ የወንዝ ዳርቻና የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቮች ለውጤቱ መገኘት ጉልህ ድርሻ አንዳላቸው አመልክተዋል። ባለፉት ስድስት ወራት የአካባቢ ቁጥጥር ሥርዓትን ለማጠናከር የወጡ ሕጎችና መመሪያዎች ተፈጻሚነት ላይ ተከታታይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መሠራታቸውንም አንስተዋል። በዚህም የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ፣ በአካባቢ ማኅበራዊ ተጽዕኖ ግምገማ እንዲሁም በብዝኃ ሕይወት ጥበቃ ላይ የተሻለ ውጤት መምጣቱን አንስተዋል።
በተፋሰስ ልማት ስራ የአፈር ለምነት በመጨመሩ የአርሶአደሮች ምርታማነት አድጓል
Jan 28, 2026 189
ወላይታ ሶዶ ፤ ጥር 20/2018 (ኢዜአ)፡- በተፋሰስ ልማት ስራ የአፈር ለምነት በመጨመሩ ምርታማነታቸው ማደጉን በወላይታ ዞን የኦፋ ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ። "እመርታ በተቀናጀ ተፋሰስ ለብልፅግናችን!" በሚል መሪ ሃሳብ የ2018 ዓ.ም ዞናዊ የተቀናጀ ተፋሰስ ልማት የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዞኑ ኦፋ ወረዳ ቡሻ ቀበሌ ጋዬ ንዑስ ተፋሰስ ላይ ተካሄዷል። በወቅቱም ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ አርሶ አደሮች እንዳሉት፤ በተፋሰስ ልማት ስራው የአፈር ለምነት በመጨመሩ ምርታማነታቸው አድጓል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል አርሶ አደር በቀለ ቶጋ፤ ለበርካታ ዓመታት በተፋሰስ ልማት ስራ ላይ ሲሳተፉ መቆየታቸውን ገልፀው በአካባቢው የልማት ስራው ከመከናወኑ በፊት በነበረው የአፈር በጎርፍ መሸርሸር ሳቢያ መሬቱ ተራቁቶ እንደነበር ገልጸዋል። ሆኖም ባለፉት ዓመታት የተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የአፈር ለምነት እንዲጨምርና ምንጮች እንዲፈልቁ በማድረጉ በስራው በዘላቂነት እንድንሳተፍ መነሳሳትን ፈጥሮልናል ብለዋል። የአየር መዛባትና የአካባቢ መራቆት ከሁሉም በላይ አካል ጉዳተኞች ላይ የሚያደርሰው አሉታዊ ተጽዕኖ የከፋ በመሆኑ አካል ጉዳተኝነት ሳይበግረኝ የሚጠበቅብኝን እየተወጣሁ እገኛለሁ ያሉት ደግሞ አርሶ አደር መሰለ መንገሻ ናቸው። የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው ከዚህ ቀደም የተራቆቱ አካባቢዎች አገግመው ምርት እንዲሰጡ ከማድረጉም ባሻገር ለኑሮ ምቹ አካባቢን ፈጥሮልናል ብለዋል። የአፈር ለምነት በጨመረባቸው እና ምንጭ በፈለቀባቸው አካባቢዎች የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን በማምረት ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ተናግረዋል። የኦፋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዲሱ ወርቁ በበኩላቸው፤የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ለዘላቂ የግብርና ልማት ወሳኝ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በወረዳው በዘንድሮ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ሥራ ከ31 ሺህ በላይ ህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ በ20 ንዑስ ተፋሰሶች ከ2 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት መታቀዱን ገልጸዋል። በዞኑ ባህል ሆኖ የቀጠለው የተፋሰስ ልማት ስራ በስነ-አፈር እና በስነ-አካላዊ ስራዎች የተራቆቱ አካባቢዎች በማገገማቸው ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዘማች ሶርሳ (ዶ/ር) ናቸው። ይህንን ውጤት ለማስቀጠል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በዘንድሮ የተፋሰስ ልማት ስራ በዞን ደረጃ በ315 ተፋሰሶች ከ46 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት ለመሸፈን ታቅዶ ስራ መጀመሩን ነው የገለጹት። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የወላይታ ዞን ብልጽግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አማረ አቦታ (ዶ/ር)፤ በዞኑ የተፋሰስ ልማት ስራ ከተጀመረ ወዲህ የተራቆተ መሬት በማገገሙ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በተገቢው ማስረጽ እንደሚገባ ገልጸው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ስራ በመሳተፍ ኃላፊነቱን እንዲወጣም አሳስበዋል።
በመጪው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞች ዝግጅት ተጠናክሮ ቀጥሏል
Jan 27, 2026 130
ጊምቢ፤ ጥር 19/2018(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ዝግጅት ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። በኦሮሚያ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር አካል የሆነው የችግኝ ዝግጅት ስራ በተለያዩ ዞኖች በሰፊው እየተካሄደ ይገኛል። በምዕራብ ወለጋ ዞንም ከበጋ ወራት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ ጎን ለጎን የችግኝ ዝግጅት በሰፊው እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል። በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፍቅሩ ብርሃኑ እንደገለጹት፤ በመጪው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ዝግጅት በስፋት እየተከናወነ ነው። እየተዘጋጁ ከሚገኙ ችግኞች መካከል አብዛኛዎቹ ለምግብነት የሚውሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች ሲሆኑ ለደን እና ለውበት አገልግሎት የሚውሉ ችግኞችም እየተዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም የአቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ማንጎ፣ ሙዝና የአናናስ ችግኞች በስፋት እየተዘጋጁ መሆኑን አንስተው ችግኞቹ የሚተከሉት በ66 ሺህ 827 ሄክታር መሬት ላይ መሆኑንም ገልጸዋል። የችግኝ ዝግጅቱ እየተደረገ ያለው ከ2 ሺህ 900 በላይ በሆኑ የመንግስትና የግል ችግኝ ማፊያ ጣቢያዎች መሆኑን ጠቅሰው በችግኝ ዝግጅት ስራው ከ3 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በአጠቃላይ በዞኑ ከ3 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ለተከላ እየተዘጋጁ መሆኑን አስረድተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ሀገራት ለውኃ አቅርቦት፣ ጥራት እና ለንጽህና መሰረተ ልማቶች ቅድሚያ መስጠት ይጠበቅባቸዋል
Feb 1, 2026 138
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ሁሉም ሀገራት ለውኃ አቅርቦት፣ ለጥራት እና ለንጽህና መሰረተ ልማቶች ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው የአፍሪካ ሕብረት አስገነዘበ። በሕብረቱ የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና የዘላቂ አካባቢ ጥበቃ ኮሚሽነር ሙሴ ቪላካቲ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ አህጉራዊው የግብርና ልማት ፕሮግራም ባለፉት 20 ዓመታት በአባል ሀገራት ዘንድ ጉልህ ለውጦች ማምጣቱን ገልጸዋል። ይህም አባል ሀገራት ጠንካራ የግብርና ዕቅድ ሥርዓት እንዲዘረጉ፣ ውጤታማ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም ቀረፃ እንዲኖራቸው እና በምርትና ምርታማነት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማገዙን አንስተዋል። ፕሮግራሙ ትኩረት የሚያደርገው በተለይም በምርት መጠንና በምርታማነት ዕድገት ላይ በመሆኑ፤ በአሁኑ ወቅት በበርካታ ሀገራት ውስጥ የሚታየው የምርት መጠን መጨመር የዚሁ ጥረት ውጤት ነው ብለዋል። ማንኛውም የልማት እንቅስቃሴ ከውኃ ጋር የተቆራኘ መሆኑን አስገንዝበው፤ ግብርናን፣ ኢነርጂን ወይም ጤናን ስናስብ ሁሉም ነገር ከውኃ ጋር የተያያዘ ነው፤ ስለዚህ ውኃ ለዘላቂ ልማት እጅግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ነው “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የሚለው መሪ ሐሳብ ለ39ኛው የሕብረቱ መሪዎች ጉባዔ የተመረጠው ብለዋል። ኮሚሽነሩ ጉዳዩ በሕብረቱ አጀንዳነት የተያዘው በአህጉሪቱ ያለውን የውኃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል። በአህጉሪቱ ወደ 400 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች መሰረታዊ የውኃ አገልግሎት እንደማያገኙ ጠቁመው፤ ከ700 ሚሊየን የሚልቁትም ደኅንነቱ የተጠበቀ የጽዳት አገልግሎት የላቸውም ብለዋል። ይህ የአገልግሎት እጥረት በሰዎች የዕድገትና የአህጉሪቱ የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ላይ ትልቅ እንቅፋት መሆኑንም አመላክተዋል። ውኃን እንደ ትምህርት፣ ጤና እና ግብርና ትልቅ ትኩረት ሰጥተን ብንሠራበት ኖሮ ይህንን ችግር በቀላሉ መፍታት እንችል ነበር ያሉት ኮሚሽነሩ፤ አሁን ላይ ጉዳዩ ትኩረት በማግኘቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ ዋነኛ ግብ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መሆኑን ተናግረው፤ የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮግራም 45 በመቶ የሚሆነውን የግብርና ምርት በአፍሪካ ለማምረት ግብ ይዞ እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል። በተጨማሪ የአፍሪካን የውኃ አካላት ሀብት ወይም ብሉ ኢኮኖሚን ሙሉ በሙሉ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሆነ አንስተው፤ ይህ ዘርፍ ለአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራና ለኢኮኖሚ መነቃቃት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበታል ነው ያሉት። የአፍሪካን የሰብል ዝርያዎች መጠበቅ መቻል የአህጉሪቱ ኅልውና ጉዳይ መሆኑን ኮሚሽነሩ ገልጸው፤ ለዚህም ጠንካራ የዘር ባንኮች ሊኖሩን ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
አጀንዳ 2063 በአፍሪካውያን ኑሮ ላይ የሚጨበጥ ለውጥ እንዲያመጣ ማድረግ ይገባል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Jan 31, 2026 74
አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ከአህጉራዊ ራዕይ ባለፈ የዜጎችን ኑሮ የሚቀይር ፕሮጀክት ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ አሳሰቡ። የአጀንዳ 2063 ትግበራ የሚከታተለው የሚኒስትሮች ኮሚቴ ዛሬ ስብሰባውን በበይነ መረብ አድርጓል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት አዲሱ የህብረቱ አመራር አጀንዳ 2063 ውጤታማ ለማድረግ ከቃል የተሻገረ የፖለቲካ ቁርጠኝነትን በመላበስ አበክሮ መስራት ይገባዋል። የአጀንዳ 2063 የ10 ዓመት የሁለተኛ ምዕራፍ የትግበራ እቅድ አህጉራዊውን ማዕቀፍ ለማፋጠን የሚያስችል ግልጽ ፍኖተ ካርታ እንዳለው አመልክተዋል። ይሁንና አነስተኛ የፋይናንስ አቅርቦት፣ የትላልቅ ፕሮጀክቶች መጓተት እና የተቋማዊ አቅም ውስንነት የሚፈለገውን ውጤት አለማስገኘቱን ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ ራዕይን ከፋይናንስ አቅርቦት፣ እቅድን የመፈጸም አቅምን ከመጨመር እና ክትትልን ከተጠያቂነት ጋር ማስተሳሰር ይገባል ነው ያሉት። የአስተዳደር ሪፎርሞች ማጠናከር እና የፖሊሲ ማነቆዎችን ማስቀረት ቁልፍ እንደሆነም አንስተዋል። የአፍሪካ ሀገራት ከአጀንዳ 2063ትን የአፍሪካውያን የዕለት ተዕለት ኑሮ ወደ መቀየር ምዕራፍ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ሊቀ መንበሩ ማሳሰባቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ የማግኘት የጋራ ፍላጎት ታሪካዊ ፍትህን የሚያሰፍን ነው - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Jan 27, 2026 155
አዲስ አበባ፤ ጥር 19/2018(ኢዜአ):- የአፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ አባል የመሆን የጋራ መሻት ታሪካዊ ፍትህን ማስፈንና እኩልነትን ማረጋገጥ እንደሚያስችል የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። አፍሪካ ለዘመናት ቋሚ ውክልና አለማግኘቷ የምክር ቤቱን ተአማኒነት ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው ሲሉም ተናግረዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ከፍተኛ ደረጃ የህዝብ የክርክር መድረክ ትላንት ማምሻውን አድርጓል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት በበይነ መረብ ባደረጉት ንግግር አፍሪካ የዓለም ፈተናዎች በተናጠል እንደማይፈቱ በጽኑ ታምናለች ብለዋል። ሊቀ መንበሩ ዓለም አቀፍ ህግ ከታሪክ ግንዛቤ ጋር በተሰናሰለ መልኩ መተግበር አለበት ያሉ ሲሆን በተለይም የቅኝ ግዛት እና የመዋቅራዊ ኢ-ፍትሃዊነት አሻራዎች የተለየ ትኩረት እንደሚያሻቸው አመልክተዋል። ዩሱፍ አፍሪካ ለሰላም ያላት ቁርጠኝነት ተጨባጭ መሆኑን ገልጸው በሰላም አስከባሪ አስተዋጽኦዎች፣ የጸጥታ አካላት የህይወት መስዋዕትነቶችን በመክፈል፣ ከኃይል ይልቅ ለሕጋዊ ስርዓት መስፈን በቁርጠኝነት በመስራትና የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር በሰላም ጉዳይ ያለውን ጠንካራ አጋርነት በማሳያነት ገልጸዋል። አፍሪካ ለዓለም ሰላም እና ደህንነት መረጋጋጥ ብዙ ብታበረክትም አሁን በዓለም መድረክ ላይ ባላት ውክልና ላይ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳይ መሰረታዊ ችግር ሆኖ መቀጠሉንም ነው የተናገሩት። 55 ሀገራት እና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ህዝብ የያዘችው አፍሪካ 80 ዓመታትን ባስቆጠረው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታ ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ አለማግኘቷ ኢ-ፍትሃዊ ብቻ ሳይሆን የምክር ቤቱን ተአማኒነት ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው ብለዋል። የአፍሪካ የጋራ ፍላጎት በምክር ቤቱ ቋሚ ውክልና ከነሙሉ መብቶቿ ማግኘት ነው ያሉት ሊቀ መንበሩ ይህም እኩልነት፣ በዓለም ስርዓት ውስጥ ውጤታማነትና ታሪካዊ ፍትህ እንዲሰፍን ያደርጋል ሲሉ መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኢጋድ የ40 ዓመታት ጉዞ፤ ከድርቅ አደጋ ምላሽ ሰጪነት እስከ ቀጣናዊ ትስስር ተዋናይነት
Jan 21, 2026 306
በሙሴ መለሰ ምስራቅ አፍሪካ በአፍሪካ አህጉር በየጊዜው ከፍተኛ ለውጥ የሚያስተናግድ እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ቀጣና ነው። ከ300 ሚሊየን በላይ ህዝብ የሚኖርበት ይህ ቀጣና ከፍተኛ የሰው ሀብት ያለው ሲሆን ፈጣን የወጣት ህዝብ እድገት እና የገበያ ተደራሽነት መስፋት እየታየበት ይገኛል። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የምስራቅ አፍሪካ አጠቃላይ ዓመታዊ ጥቅል ምርት(ጂዲፒ) እ.አ.አ በ2025 598 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር መድረሱን ገልጿል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ያሉ ሀገራት የሚገኙበት ቀጣና ነው ምስራቅ አፍሪካ። ምስራቅ አፍሪካ ግብርና፣ ቁም እንስሳት፣ ኢነርጂ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ንግድ፣ ትራንስፖርት፣ የኢኮኖሚ ኮሪደሮች እና በፍጥነት እያደገ የመጣው ዲጂታል ኢኮኖሚ እምቅ የኢኮኖሚ አቅሞቿ ናቸው። ከመልክዐ ምድራዊ አቀማመጥ አንጻርም የኢትዮጵያ ከፍታማ ስፍራዎች፣ የታላላቅ ሀይቆች ተፋሰስ እና የአፍሪካ ቀንድ ዝቅተኛ ቦታዎች ይጠቀሳሉ። ከቀይ ባህር እስከ ህንድ ውቅያኖስ ምስራቅ አፍሪካን የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የዓለም የማሪታይም ንግድ መተላለፊያ መስመሮች ይገናኙባታል። ይህ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ ምስራቅ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ንግድ፣ ሎጂስቲክስ እና ጂኦ ፖለቲካ ውስጥ ያላትን ሚና አሳድጓል። ቀጣናው ለመረጋገት እና ለትብብር ያለው ጠቀሜታም በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ለብዙ ክፍለ ዘመናት በምስራቅ አፍሪካ የሚገኙ የተለያዩ ማህበረሰቦች በንግድ፣ በፍልሰት እና የባህል ትስስር ተጋምደዋል። በዘመናዊው ዓለም ይህ ታሪካዊ ትስስር ለቀጣናዊ ትስስር ጠንካራ አስተዋጽኦ ያለው ነው። በሀገራት በጋራ የሚገነቡ መሰረተ ልማቶች፣ የተሳናሰኑ ፖሊሲዎች እና የሰዎችና እቃዎች ነጻ ዝውውር የኢኮኖሚ እድገት እና አጠቃላይ ልማትን የሚያሳልጥ ነው። ቀጣናዊ ትስስር የተበታተነ ገበያ ወደ አንድ ማዕቀፍ ለማምጣት፣ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ዜጎች በተለይም ወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አኳያ አስተዋጽኦወ ቁልፍ ነው። ምስራቅ አፍሪካ እንደ እድሎቹ ሁሉ በርካታ ፈተናዎች ያሉበት ቀጣና ነው። በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚፈጠረው ድርቅ እና ጎርፍ፣ ግጭት፣ መፈናቀል እና የልማት ተደራሽነት ፍትሃዊ አለመሆን በዋናነት የሚነሱ ጉዳዮች ናቸው። እነዚህ ድንበር ተሻጋሪ ፈተናዎች ከተናጠል ይልቅ የጋራ የተግባር ምላሽ ይፈልጋሉ። ፈተናዎችን ከግምት በማስገባት በቀጣናው በተደጋጋሚ ለሚከሰተው ድርቅ እና የከባቢ አየር ችግር የተቀናጀ ምላሽ መስጠት የሚያስችለው ተቋማዊ ማዕቀፍ ከ40 ዓመታት በፊት ወደ ስራ ገባ። ይህ ተቋም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ነው። የኢጋድ መቋቋም እርሾ በወቅቱ በቀጣናው ያጋጥሙ የነበሩ ቀውሶች ናቸው። እ.አ.አ በ1980ዎቹ መጀመሪያ በቀጣናው የነበረው ድርቅ እና ረሃብ የብዙ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈ ሲሆን ይህም ቀጣናው ለአየር ንብረት ለውጥ ያለውን ተጋላጭነት በግልጽ የሚያሳይ ነው። አደጋዎቹ ድንበር ተሻጋሪ በመሆናቸው የተቀናጀ የጋራ ምላሽ የሚፈልጉ ናቸው። ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን እና ዩጋንዳ ለአንገብጋቢው ቀጣናዊ ጉዳይ ምላሽ በመስጠት ኢጋድን እ.አ.አ በ1986 አቋቋሙ። ኢጋድ በወቅቱ ሲቋቋም ዋነኛ የስራ ድርሻው የነበረው ድርቅ፣ በረሃማነት እና ሁለቱ የሚያደርሷቸውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽእኖዎችን ለመከላከል የሚደረጉ ቀጣናዊ ጥረቶችን ማስተባበር ነው። ይሁንና የከባቢ አየር ፈተናዎቹ ከፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ግጭት እና ካለመልማት ጋር ጥልቅ ቁርኝት ያላቸው መሆኑ አድማሱ የሰፋ ግብ ያለው ቀጣናዊ ተቋምን መፍጠር እንደሚያስፈልግ በወቅቱ ይነሳ ነበር። በዚሁ መሰረት ኢጋድ እ.አ.አ በ1996 በድጋሚ አደረጃጀቱ ተስተካክሎና የስራ ድርሻው ሰፍቶ እንደገና ተቋቋመ። ከድርቅ እና ከባቢ አየር ጉዳዮች በመሻገር ኢጋድ ሰላም እና ደህንነትን ማረጋገጥ፣ የኢኮኖሚ ትብብር እና ትስስር እንዲሁም ቀጣናዊ ትስስርን ማጎልበት የተቋሙ ቁልፍ የትኩረት መስኮች ሆነዋል። የኢጋድ ዋና መቀመጫ ጅቡቲ ነው። የሰፋው የስራ ድርሻ ኢጋድን በአፍሪካ ቀንድ የምክክር፣ የውይይት እና የተቀናጀ ልማት የጋራ ማዕቀፍ እንዲሆን አድርጎታል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) እ.አ.አ በ2026 የተመሰረተበትን 40ኛ ዓመት እንደሚያከብር ከሰሞኑ አስታውቋል። ኢጋድ በአራት አስርት ዓመታት ውስጥ በስኬት ደረጃ ሊነሱ የሚችሉ ተግባራትን አከናውኗል። ከሰላም እና ደህንነት አንጻር ኢጋድ በቀጣናው ውስብስብ የሚባሉ ግጭቶች በእርቅ እና በውይይት እንዲፈቱ አስተዋጽኦ አድርጓል። ለዓመታት በሱዳን ሲካሄድ የነበረውን የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲያበቃ እ.አ.አ በ2005 ሁሉን አቀፍ የሰላም ስምምነት እንዲፈረም በሰላም ሂደት ውስጥ የድርሻውን ተወጥቷል። ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ደቡብ ሱዳን በህዝበ ውሳኔ ራሷን የቻለች ሀገር ሆናለች። ኢጋድ በሶማሊያ የሰላም ጥረቶች ቁልፍ ተዋናይ ነበር። በሶማሊያ የፖለቲካ እርቅ እና መረጋጋት እንዲፈጠር ሲከናወኑ በነበሩ ስራዎች ላይ ተሳትፎ አድርጓል። ቀጣናዊ ተቋሙ ባለው የእርቅ የስራ ክፍል ግጭቶች እንዳይከሰቱና ከተከሰቱም እንዲፈቱ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣም ይገኛል። ከተቋቋመበት የስራ ድርሻ አኳያ ኢጋድ በምግብ ደህንነት፣ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና አደጋ ስጋት አስተዳደር ላይ ሰፋፊ ተግባራትን አከናውኗል። ለአብነትም የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያና ትግበራ ማዕከል (ICPAC) የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓቶችን በማጠናከር፣ በአየር ትንበያዎች እና የፖሊሲ ድጋፎች አማካኝነት አባል ሀገራት ለድርቅ እና ጎርፍ አደጋዎች ምላሽ እንዲሰጡ የድርሻውን እየተወጣ ይገኛል። ይህም ቀጣናዊ የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽን ለማጠናከርና የመንግስታትን አቅም ከመገንባት አኳያ ትልቅ ድርሻ እንደተወጣ ማዕከሉ ይገልጻል። ከኢኮኖሚ ትብብር እና ቀጣናዊ ትስስር አኳያም ኢጋድ ድንበር ተሻጋሪ ንግድ እንዲያድግ፣ መሰረተ ልማት እንዲስፋፋና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እንዲጠናከሩ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በትራንስፖርት ኮሪደሮች፣ በአርብቶ አደሮች እንቅስቃሴዎችና ቀጣናዊ ገበያዎች ላይ ኢኒሼቲቮችን በመቅረጽ በአባል ሀገራት እንዲተገበር ከማድረግ ባለፈ ድጋፉን እየሰጠ ነው። ኢጋድ በቀጣናው ለንግድ እና ለእንቅስቃሴ የሆኑ መሰናክሎች እንዲቀንሱ አስተዋጽኦ አድርጓል። ኢጋድ ከፍልሰተኞች ና ተፈናቃዮች ጋር ያሉ ችግሮች እንዲፈቱና ጉዳዩ ከፈተና ባለፈ የልማት እድል እንደሆነ በማንሳት ሁሉን አቀፍ እይታ እንዲፈጠር እየሰራ ይገኛል። በአራት አስርት ዓመታት ውስጥ ኢጋድ ተቋማዊ አቅሙን በማጠናከርና አጋርነቱን በማስፋት ረገድ የተለያዩ ስራዎችን አከናውኗል። ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ከሌሎች ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር እየሰራ ነው። ተቋሙ በቴክኒካዊ እና ፖለቲካዊ ደረጃዎች ለአባል ሀገራት ቋሚ የምክክር ማዕቀፍ ሆኖ እያገለገለ ሲሆን ይህም በሀገራት መካከል የጋራ መተማመንና የጋራ መግባባት እንዲኖር ያለው አስተዋጽኦ ወሳኝ የሚባል ነው። የኢጋድ የ40 ዓመታት ጉዞ በስኬቶች ብቻ የታጀበ አይደለም። ቀጣናዊ ተቋሙ ከፍተኛ ፈተናዎችም አጋጥመውታል። የመጀመሪያው በተደጋጋሚ ጊዜ የሚቀሰቀሱ እና ዘላቂ መቋጫ ያላገኙ ግጭቶችና የፖለቲካ አለመረጋጋቶች ናቸው። ጉዳዮቹ የኢጋድን የእርቀ ሰላም ጥረቶች ፈተና ውስጥ ከተውታል። አንዳንድ ጊዜ በአባል ሀገራት መካከል ያሉ መከፋፈሎች ኢጋድ ቆራጥ ውሳኔ እንዳይወስን ሲገድበው ታይቷል። የፋይናንስና ተቋማዊ አቅም ውስነነቶች የኢጋድ የተለያዩ ማዕቀፎች ትግበራ ላይ መስተጓጎሎችን ፈጥረዋል። ኢጋድ ከውጭ አጋሮች የሚያገኘው ፈንድ ከራስ ዘላቂ የፋይናንስ አቅርቦት ጋር ማመጣጠን አለመቻል የተቋሙን የዘላቂነት እና የባለቤትነት ጉዳይ ላይ ተጽእኖ አሳድረዋል። የፖለቲካ ተንታኞች ተቋሙ ከአባል ሀገራቱ የሚያገኝውን ጨምሮ ገቢ እና የፋይናንስ ቅሙን የሚያጠናክርባቸውን መንገዶች በሚገባ ማየት እንዳለበት ይመክራሉ። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ሌላኛው የኢጋድ ፈተና ነው። በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ደጋግመው የሚከሰቱ ድርቆች እና የጎርፍ አደጋዎች በተቋማዊ ምላሽና አቅም ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድረዋል። ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት መስፋፋትና መፈናቀል ጫናዎቹ ይበልጥ እንዲበረቱ አድርገዋል። ቀጣናዊ ስምምነቶችና የአሰራር ማዕቀፎችን ወደ ተጨባጭ የሀገራት ትግበራ የማሸጋገር ጉዳይም ትኩረት እንደሚያሻውም ይነሳል። የሀገራት የሚለያዩ የትኩረት መስኮች እና አቅሞች በቀጣናዊ ማዕቀፎች ሂደትና ትግበራ ላይ የራሳቸውን ተጽእኖ ያሳድራሉ። 40 ዓመታትን ያስቆጠረው ኢጋድ በምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ትብብር ያለውን ወሳኝ ጠቀሜታ የሚያሳይ ህያው ተቋማዊ ምስክር ነው። ለድርቅ እና ረሃብ ምላሽ ከመስጠት በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት፣ አንድነት እና ልማት ቁልፍ ተዋናይነት ተሸጋግሯል። አንድነት እና የፖለቲካ ቁርጠኝነትን በኢጋድ አባል ሀገራት መካከል ማጠናከር ለቀጣናዊ የተግባር ምላሽና ለተቋሙ ዘላቂ ውጤታማነት ወሳኝ የሚባሉ ጉዳዮች ናቸው። የአባል ሀገራት የጋራ አንድነት የተረጋገጠበት ኢጋድ ለቀውሶች ምላሽ ከመስጠት ባለፈ ለጋራ ፍላጎቶች መሳካት ያለው ሚናም ያድጋል። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ግንባታና ዘላቂ ልማት ላይ ቀጣይነት ባለው መልኩ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ የኢጋድ የትኩረት አጀንዳ ሊሆን ይገባል። የኢጋድ የሰላም እና መረጋጋት ጥረቶች በሁሉን አቀፍ አስተዳደር፣ በወጣቶችና ሴቶች የነቃ ተሳትፎ እንዲሁም በዘላቂ የሀገር ግንባታ አካሄዶች ሊደገፍ እንደሚገባ የፖለቲካ ባለሙያዎች ምክረ ሀሳባችውን ያስቀምጣሉ። የልማት ፍላጎት አለመሟላት እና የኑሮ ውድነትን ለግጭቶች አበይት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን ከስር መሰረቱ መፍታት ለዘላቂ መረጋጋት ወሳኝ ነው። ኢጋድ የተጣለበትን ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር እውን የማድረግ ኃላፊነቱን የበለጠ ለመወጣት የመሰረተ ልማት ትስስሮች ማጠናከር፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እውን ማድረግና በቀጣናው በፍጥነት እያደገ ለመጣው ዜጋ የስራ ፈጠራና እድሎችን የሚያሰፉ ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶችን የማስፋት ስራ ላይ አበክሮ መስራት ይኖርበታል። ፈተናዎች እንዳሉ ሆነው የኢጋድ የ40 ዓመታት ጉዞ የሚያሳየው አንድ ግልጽ ሀቅ አለ። ይህም እውነታ የምስራቅ አፍሪካ መጻኢ ጊዜ እርስ በእርስ መተሳሰርና በትብብር መቆም እንደሆነ ነው። የተቋቋመበትን አላማ ዳግም ቃል ኪዳኑን በማደስ በቁርጠኝነት መስራት ከቻለ፣ ተቋማዊ አቅሙን በሚገባ ካጎለበተ፣ በሀገራት መካከል አጋርነትና ትብብርን ካጠናከረና የዲጂታል ዘመን በሚገባ በመዋጀት ከሰራ ኢጋድ ቀጣዩ ትውልድ ሰላማዊ፣ አይበገሬናና የበለጸገ ቀጣና እንዲረከብ በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና መጫወቱን መቀጠል ይችላል።
ሐተታዎች
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 359
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ። በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 714
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 663
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 877
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 708
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 678
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 1282
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3600
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3253
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2104
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7914
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6400
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት
Jan 14, 2026 379
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት ብርቱዎች ነገን በማሰብ ሁሌም ታትረው ይሰራሉ፤ ይደክማሉ፤ ይጥራሉ…ለቀጣዩ ትውልድም ጥሪት በማስቀመጥ አሻራቸውን ያኖራሉ። አገር የምትገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው። “አባት ያበጀው፤ ለልጅ ይበጀው” እንደሚባለው ልጆች ከአባቶቻቸው ያገኙትን ጥሪት በአዲስ እውቀትና አሰራር ለአገር እድገት በሚበጅ መልኩ አጠናክረው መጠቀማቸው አይቀርም። “ዕድሜ ጸጋ ነው” የሚለው አባባል አንዳንዴ በዕድሜ ብንገፋም ጠንክረን ከሰራን ብዙ ነገር እናያለን ከሚለው ጋር የተያያዘ ነው። በሰቆጣ ከተማም እድሜ ሳይገድባቸው በልማት ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ለዚህ ማሳያ ናቸው። የከተማዋ ነዋሪ የ67 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ አወቀ እና የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ዕድሜያቸው ቢገፋም ጠንክሮ ከተሰራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና ዕድሜ ጸጋ ሆኖ ብዙ ለውጥ ማየት እንደሚቻል ማሳያ ናቸው። ግለሰቦቹ ከዕድሜ ብዛት ጉልበቴ ደከመ፣ አይኔ ፈዘዘ፣ እጄም ተሳሰረ…ሳይሉ ጊዜያቸውን በደን፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ በማሳለፍ ለወጣቶች የልማት አርአያነት ያለው ተግባር እየፈጸሙ ነው። አቶ ብርሃኑ አወቀ በሰቆጣ ከተማ ዳርቻ የሚገኝ አለቱ ያገጠጠና የተራቆተ አካባቢን ከሌላ አካባቢ ለም አፈር በማምጣትና በመደልደል አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ደን በማልማት ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ነው። ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከወጣሁ ጀምሮ ጠንክሬ በመስራት የምለወጥበትን ሥራ ማሰብ ስነበረብኝ፤ የቆሻሻ መጣያ ሆኖ ለዘመናት የቆየን ጭንጫ መሬት ጠርጌና ደልድዬ ማልማት ችያለሁ ይላሉ ወደኋላ መልስ ብለው የተነሱበትን ሁኔታ ሲያስታውሱ። ግማሽ ሄክታር በማይሞላ መሬት ላይ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ዘይቱና፣ ጌሾ፣ ቡና፣ ማንጎና አቮካዶ አልምተዋል። በተጨማሪም ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመንና ሽንኩርት በማምረት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ጥሪት አፍርተዋል። ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ተግቶ መስራት ከተቻለ ሀብት ማፍራትና ህይወትንም መለወጥ እንደሚቻል የገለጹት አቶ ብርሀኑ፣ ወጣቱም ከእሳቸው የሥራ ትጋት በመማር በአካባቢው ያለውን ፀጋ ለይቶ በማልማት ሊጠቀም ይገባል ሲሉ ይመክራሉ። ሌላው የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ባለፉት 18 ዓመታት በተሰማሩበት የአትክልትና ደን ልማት ሥራ የአካባቢያቸውን ገጽታ ቀይረዋል። የዕድሜ ዘመናቸውን በውትድርናና በመንግስት ሠራተኝነት በማገልገል ሃገራዊ ግዳጃቸውን ሲወጡ ነው የቆዩት። ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከተገለሉ በኋላም ቤት ውስጥ መቀመጥን አልመረጡት። አካፋና ዶማቸውን ይዘው ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ ጌሾ፣ ዘይቱና እና ማንጎ በማልማት ምርቱን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። በአካባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ለይተን ማልማት ከቻልን ድህነትን ማስወገድ የሚከብድ አይሆንም ያሉት አቶ ታደሰ፣ የተራቆተና በጎርፍ የተጎዳን መሬት በማልማት አካባቢውን ሳቢና ማራኪ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት። ወጣቱም ከእሳቸው አርአያነት ያለው ተግባር በመማር በአካባቢው እጁ ላይ ባለ ሀብት ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል በተግባር ማሳየት እንዳለበት መክረዋል። የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ እንደገለጹት፤ በብሔረሰብ አስተዳደሩ 24ሺህ 847 አርሶ አደሮች በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተዋል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል ዕድሜ ሳይገድባቸው ወደ ልማት የገቡ አረጋዊያን እያከናወኑት ያለው የግብርና ልማት ሥራ ለወጣቱ ትልቅ ትምህርት እንደሚሆንም ተናግረዋል። ከእነሱ ልምድ በመውሰድ በዞኑ ወጣቶች፣ ሴቶችና አረጋዊያን በጓሮና ባላቸው መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲያለሙ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ይህም በዞኑ የሚስተዋለውን የስርዓተ ምግብ ችግር ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።
ከማላጋ እስከ አፍሪካ ዋንጫ፤ የሞሮኮው አዲስ እንቁ ብራሂም ዲያዝ
Jan 13, 2026 385
የግል ክህሎት፣ ፈጣን አስተሳሰቡ እና በጠባብ ክፍተቶች ውስጥ ሰብሮ የመግባት አቅሙ ሙገሳ እንዲጎርፍለት አድርጓል። አንድ ለአንድ ሲገናኝ ተከላካዮችን በፈጣን አካላዊ ቅልጥፍና እና በድንገት አቅጣጫ በመቀየር የሚያልፍበት መንገድ እንዲሁም የመፍጠር አቅሙ የተመልካቾችን ቀልብ የሚይዝ ነው። የአማካይ እና የአጥቂ መስመርን በማገናኘት እና በአስገራሚ ሁኔታ አጭር ኳሶችን በማቀበልም የተዋጣለት ተጫዋች ነው ማለት ይቻላል። በቦታ አያያዙ የእግር ኳስ ልኅቀቱ ከፍተኛ ነው የሚል አድናቆት ከእግር ኳስ ባለሙያዎች አግኝቷል። ኳስን ሲያንከባልልም ለዐይን ይስባል። ከክህሎቱ እና ከማራኪ እንቅስቃሴው ባለፈ ወደ ኋላ እየመለሰ ተከላካዮችን ያግዛል፣ ኳስ ይነጥቃል። ይህ ተጫዋች የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ክስተት የሆነው የሞሮኮው ብራሂም ዲያዝ ነው። የ26 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ዲያዝ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አምስት ጨዋታዎችን አድርጎ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ነው። አዘጋጇ ሞሮኮ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ መክፈቻ ኮሞሮስን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የውድድሩን የመጀመሪያ ግብ አስቆጥሯል። ብራሂም አብዱልቃድር ዲያዝ የተወለደው እ.አ.አ ኦገስት 3 ቀን 1999 በስፔን ማላጋ ግዛት ነው። እናቱ ስፔናዊ አባቱ ሞሮኳዊ ናቸው። ዲያዝ ያደገው በማላጋ ነው። እግር ኳስንም በአንዳሉሺያዊቷ ከተማ ሲጫወት ቆይቷል። በ16 ዓመቱ ካደገበት ማላጋ በመውጣት እ.አ.አ በ2015 ወደ ማንችስተር ሲቲ ወጣት አካዳሚ በ200 ሺህ ፓውንድ ወጪ ተዘዋወረ። ዲያዝ እ.አ.አ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2016 በካራባኦ ካፕ (በቀድሞ አጠራሩ ሊግ ካፕ) ማንችስተር ሲቲ ከስዋንሲ ሲቲ ባደረገው ጨዋታ በ80ኛው ደቂቃ በኬሌቺ ኢናቺዩ ተቀይሮ በመግባት ለውኃ ሰማያዊዎቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያውን ጨዋታ ካደረገ ከሶስት ቀናት በኋላ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለሶስት ዓመታት የሚያቆየውን ፕሮፌሽናል ኮንትራት ተፈራርሟል። እ.አ.አ ኖቬምበር 21 ቀን 2017 ማንችስተር ሲቲ ከፌይኖርድ ሮተርዳም ጋር ባደረገው የሻምፒዮናስ ሊግ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል። በወቅቱ ብራሂም ስተርሊን መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ሰዓት ላይ ነበር ተቀይሮ የገባው። ዲያዝ በውኃ ሰማያዊዎቹ ማልያ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የተጫወተው እ.አ.አ ዲሴምበር 19 ቀን 2017 ነው። ማንችስተር ሲቲ ከሌስተር ሲቲ በካራባኦ ካፕ ጨዋታ ላይ ለ88 ደቂቃዎች ተሰልፎ ተጫውቷል። እ.አ.አ ጃንዋሪ 20 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን 3 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በወቅቱ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ያነሳ ሲሆን፤ በውድድር ዓመቱ አራት ጨዋታዎች ላይ ብቻ ተሳትፎ ያደረገው ብራሂም ዲይዝ የሜዳሊያ ሽልማት አግኝቷል። እ.አ.አ ኦገስት 5 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ቼልሲን 2 ለ 0 ባሸነፈበት የኮሙዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ላይ በፊል ፎደን ተቀይሮ በመግባት ለ15 ደቂቃዎች ተጫውቷል። ዲያዝ እ.አ.አ 2018/19 ማብቂያ ላይ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የመጀመሪያ ግቦቹን ለሲቲ አስቆጥሯል። በማንችስተር ሲቲ ያለው ውል እ.አ.አ 2019 ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት ስሙ ከዝውውር ጋር በስፋት ይነሳ ነበር። ዲያዝ እ.አ.አ ጥር 2019 በ17 ሚሊዮን ዩሮ ከማንችስተር ሲቲ ወደ ሪያል ማድሪድ ተዘዋወረ። ለስድስት ዓመታት የሚያቆየውን ውልም ፈርሟል። የክንፍ ተጫዋቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን በነጮቹ ማልያ ያደረገው እ.አ.አ ጥር 9 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ ሌጋኔን በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ 3 ለ 0 ባሸነፈበት ወቅት ነው። ከአራት ቀናት በኋላ በስፔን ላሊጋ ሪያል ማድሪድ ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ ተቀይሮ በመግባት በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያ ግቡን ለማስቆጠር ሶስት ወራትን ጠብቋል። እ.አ.አ ግንቦት 12 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ በላሊጋው በሪያል ሶሲዬዳድ 3 ለ 1 ሲሸነፍ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በወቅቱ ዲያዝ ስድስት ጨዋታዎች ላይ በላሊጋው የተጫወተ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ዓመቱ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ሪያል ማድሪድ እ.አ.አ በ2021/21 የውድድር ዓመት ብራሂም ዲያዝ ወደ ኤሲ ሚላን በውሰት ማምራቱን ይፋ አደረገ። ዲያዝ ሚላን እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2020 ክሮቶኔን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ የመጀመሪያ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ ግንቦት 2021 ኤሲ ሚላን ጁቬንቱስን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ያስቆጠረው ግብም ተጠቃሽ ነው። ዲያዝ በኤሲ ሚላን የውሰት ውሉ ሲያበቃ በድጋሚ ለሁለት ዓመታት በውሰት የሚቆይበት ስምምነት ሪያል ማድሪድ ከጣልያኑ ክለብ ጋር የተፈራረመ ሲሆን፤ ውሉ ሚላን ተጫዋቹን የማቆየት መብት ሰጥቶታል። እ.አ.አ መስከረም 15 ቀን 2021 ኤሲ ሚላን በሻምፒዮንስ ሊጉ የ3 ለ 2 ሽንፈት ሲያስተናግድ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ግቡን አስቆጥሯል። በ2023 ኤሲ ሚላን ቶተንሃም ሆትስፐርስን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ 1 ለ 0 ሲያሽንፍ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023 ሰኔ ወር ላይ ሪያል ማድሪድ ዲያዝ ከኤሲ ሚላን የሶስት ዓመታት የውሰት ቆይታ በኋላ ወደ ክለቡ መመለሱን አሳውቋል። ተጫዋቹ በኤሲ ሚላን ቆይታው 91 ጨዋታዎችን አድርጎ 13 ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ዲያዝ ወደ ሪያል ማድሪድ ከተመለሰ በኋላ ኮንትራቱን እስከ 2027 አራዝሟል። እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2023 ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ሪያል ማድሪድ ላስ ፓልማስን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። የክንፍ መስመር ተጫዋቹ ሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥ እና በአውሮፓ መድረክ በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ላይ ግብ በማስቆጠር እና ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ዲያዝ እስከ አሁን ለሪያል ማድሪድ ባደረጋቸው 129 ጨዋታዎች 20 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከነዚህም ውስጥ 13ቱ በላሊጋው ያስቆጠራቸው ናቸው። ከክለብ ወጣ ስንል የተጫዋቹን የብሔራዊ ቡድን ቆይታ እናገኛለን። ዲያዝ በታዳጊነቱ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ለስፔን ወጣት ቡድኖች ተጫውቷል። እ.አ.አ በ2016/17 የውድድር ዘመን ለስፔን ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በ16 ዓመቱ ተሰልፎ መጫወት ችሏል። በተለይም አዘርባጃን እ.አ.አ በ2017 ባዘጋጀችው 15ኛው የአውሮፓ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ላይ ያሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆት አስችሮታል። በዚያ ቀጥለው በነበሩ ዓመታትም ለስፔን ከ19 እና ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቷል። ብራሂም ዲያዝ በስፔን ታዳጊና ወጣት ቡድኖች ላይ በአጠቃላይ 28 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። የስፔን ታዋቂ የስፖርት ጋዜጣ ማርካ እ.አ.አ ጥር 23 ቀን 2023 ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን መጫወት ማቀዱን የሚመለከት ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ከዜግነቱ ጋር በተያያዘ ያሉ አንዳንድ የአስተደዳር ጉዳዮች በወቅቱ መፍትሄ አግኝተዋል። ይሁንና ኮትዲቯር እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሞሮኮው አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከተጫዋቹ ጋር በተደረገ የቅድሚያ ስምምነት ለተጫዋቹ ጥሪ አልተደረገለትም። ዲያዝ እ.አ.አ መጋቢት 10 ቀን 2024 ለሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሀገሪቷ ብሔራዊ መጫወት እንደሚፈልግ በይፋ ማሳወቁን ማርካ በወቅቱ ዘግቧል። ጥያቄውም ተቀባይነት አገኘ። በወቅቱ የሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ብሔራዊ ቡድኑ ከአንጎላ እና ሞሪታኒያ ጋር ለነበረበት የወዳጅነት ጨዋታ ለዲያዝ ጥሪ አድርገውለታል። እ.አ.አ መጋቢት 22 ቀን 2024 ሞሮኮ አንጎላን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። እ.አ.አ ጥቅምት 6 ቀን 2024 ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከጋቦን ጋር ባደረገችው ጨዋታ 4 ለ 1 ስታሸንፍ የመጀመሪያ ግቡን ለሞሮኮ ማስቆጠር ቻለ። እ.አ.አ ሕዳር 15 ቀን 2024 ሞሮኮ በማጣሪያው ጋቦንን 5 ለ 1 ስትረታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። ከሶስት ቀናት በኋላ ሞሮኮ ከሌሴቶ ጋር ባደረገችው የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ 7 ለ 0 ስታሸንፍ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር በሀገሩ ማልያ የመጀመሪያ ሀትሪኩን ሰርቷል። እ.አ.አ ጥቅምት 2025 ሞሮኮ ራባት ላይ ኮንጎ ሪፐብሊክን 1 ለ 0 በማሸነፍ በስፔን ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተይዞ የነበረውን 15 ተከታታይ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ክብረ ወሰን በመስበር ወደ 16 ማድረስ ችላለች። በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ ላይ ዲያዝ ተሰልፎ ተጫውቷል። የሞሮኮ ተከታታይ የማሸነፍ ጉዞ 19 ጨዋታዎች ደርሶ የነበረ ሲሆን በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከማሊ ጋር አንድ አቻ ስትለያይ አብቅቷል። ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማጣሪያ ብታልፍም አስቀድማ ውድድሩን እንድታዘጋጅ እድል አግኝታ የነበረው ጊኒ በዝግጅት ማነስ ምክንያት በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ከሁለት ዓመት በፊት አዘጋጅነቷ ተነጥቆ ለሞሮኮ ተሰጥቷል። ሞሮኮ የዘንድሮውን ውድድር በደማቅ ሁኔታ እያካሄደች ትገኛለች። በውድድሩ ላይ ጎልተው ከታዩ ተጫዋቾች መካከል ብራሂም ዲያዝ ተጠቃሽ ነው። በአፍሪካ ዋንጫው እስከ አሁን ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። በተሰለፈባቸው በእያንዳዱ ጨዋታዎች ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን በአምስት የአፍሪካ ዋንጫ ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። ሞሮኮ በሩብ ፍጻሜው ማሊን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሯል። ሀገሩ ወደ ግማሽ ፍጻሜ እንድታልፍ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱንም እየመራ ይገኛል። ሞሮኮ በዚሁ ግስጋሴዋ ከቀጠለች ዲያዝ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና ኮከብ ተጫዋች የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። ሞሮኮ በግማሽ ፍጻሜው ከናይጄሪያ ጋር ረቡዕ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ታደርጋለች። ዲያዝ በዚህ ጨዋታ ላይ ልዩነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። አንዳንድ የእግር ኳስ ተንታኞች ብራሂም ዲያዝ እ.አ.አ በ2026 ወጥነት ያለው ብቃት ማሳየት ከቻለ የአፍሪካ ኮከብ ተጫዋችነት ሽልማቱን የሚወስድበት የለም እያሉ ይገኛሉ። ሞሮኳውያን በተጫዋቹ ፍቅር ልባቸው ከንፏል። በየጨዋታው ዲያዝ ዲያዝ እያሉ ከፍተኛ ድጋፍ እና ሙገሳ እየሰጡት ይገኛሉ። እሱም በድንቅ ብቃቱ ምላሽ እየሰጣቸው ነው። በተወለደበት ማላጋ ከተማ የጀመረው የእግር ኳስ ሕይወት በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የበለጠ አብቧል። የሞሮኮው አዲሱ ኮከብ ብራሂም ዲያዝ ቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወት በስኬት እና በድል የደመቀ እንደሚሆን ከአሁኑ ድንቅ ብቃቱ ተነስቶ መናገር ይቻላል።