ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ኢትዮጵያ የባለብዙ ወገን ግንኙነቷን ለማጠናከር እና የስትራቴጂክ አጋርነቷን ለማስፋት ቁርጠኛ መሆኗን ገለጸች
Jun 30, 2025 45
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የባለብዙ ወገን ግንኙነቷን ለማጠናከር እና የስትራቴጂክ አጋርነቷን አድማስ የበለጠ ማስፋት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አስታወቀች። 10ኛው የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ (AIIB) ዓመታዊ ስብስባ በቻይና ቤጂንግ ተካሄዷል። በስብስባው ላይ የገንዘብ ሚኒስትር እና የ2024/25 የባንኩ አስተዳደሪዎች ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አሕመድ ሽዴ ተሳትፈዋል። ሚኒስትሩ ከስብስባው ጎን ለጎን ከፋይናንስ ተቋማት እና የልማር አጋሮች ጋር የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን አድርገዋል። ከተሰናባቹ የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ ጂን ሊኪን ጋር በነበራቸው ቆይታ ጂን የ10 ዓመት የአገልግሎት ቆይታቸው ባንኩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ክብር የሚሰጠው ተቋም እንዲሆን ያከናወኑትን ስራ አድንቀዋል። በውይይቱ ባንኩ ትራንስፖርት፣ ኢነርጂ እና የማዘጋጃ ቤታዊ መሰረተ ልማት ጨምሮ በኢትዮጵያ ያለውን ተሳትፎ ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል። የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከቻይና የፋይናንስ ሚኒስትር እና የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ የገዢዎች ቦርድ ሰብሳቢ ላን ፎአን፣ ከኳታር የፋይናንስ ሚኒስትር አሊ አል ኩዋሪ ጋር ተወያይተዋል። ሚኒስትሩ ከቻይና ልማት ባንክ፣ ለቻይና የኤክስፖርት እና ኢምፖርት ባንክ እና ከይና ኢንዱስትሪና ንግድ ባንክ አመራሮች ጋርም ተነጋግረዋል። ውይይቶቹ በልማት ፋይናንስ፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ማፋጠን እና የኢትዮጵያን የእድገትና የማይበገር አቅም መገንባት አጀንዳ የኢኖሼሽን አማራጮችን ተጠቅሞ መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የባለብዙ ወገን ግንኙነቷን ለማጠናከር፣ የአረንጓዴና ሁሉን አቀፍ እድገትን ለማሳለጥ እንዲሁም ለኢትዮጵያውያን እና አፍሪካ ውጤቶችን የሚያስገገኙ ስትራቴጂካዊ አጋርነቶችን ለማስፋት ቁርጠኛ መሆኗን ገልጻለች። በተጨማሪም ኢትዮጵያ የ10 ዓመት የልማት እቅዷ እና ለሰፊው ቀጣናዊ ትስስር አጀንዳዋ ድጋፍ እንዲያገኝ ከእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ እና ሌሎች ተቋማት ጋር በትብብር እንደምትሰራ የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል ያላትን የጸና ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው- ሚኒስትር አህመድ ሽዴ
Jun 30, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል እና ከባቢ አየርን ለመጠበቅ ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ። 10ኛው የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ (AIIB) ዓመታዊ ስብሰባ በቻይና ቤጂንግ ተካሄዷል። በስብሰባው ላይ የገንዘብ ሚኒስትር እና የ2024/25 የባንኩ አስተዳደሪዎች ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አሕመድ ሽዴ ተሳትፈዋል። የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ፣ የባንኩ ዓለም አቀፍ አባል ሀገራት እና ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በስብሰባው ላይ ተሳትፎ አድርገዋል። የገንዘብ ሚኒስትር እና የ2024/25 የባንኩ ገዢዎች ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አሕመድ ሽዴ በስብሰባው ላይ የኢትዮጵያ ሪፎርም እና የልማት ግቦችን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የላቀ አመራር ሰጪነት ለውጥ እያስመዘገበች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ለውጡ የተገኘው በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ እንደሆነና የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለመፍጠር፣ የግሉን ዘርፍ ኢንቨስትመንት ለማሳደግ፣ የአስተዳደር አቅምን ለማሻሻል እንዲሁም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የማይበገር እና ከወቅቱ ጋር የሚራመድ ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንዳለው አመልክተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና ከባቢ አየርን ለመጠበቅ ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያመላክት ነው ብለዋል። የኢኮኖሚ ሪፎርሙ እና የአረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ፈተናዎች ሁሉን አቀፍ፣ ጊዜው የደረሰባቸው የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል አማራጮች እና ሀገር በቀል መፍትሄዎችን ለማበጀት ያላትን የአመራር ቁርጠኝነት አንስተዋል። የገንዘብ ሚኒስትር እና የ2024/25 የባንኩ አስተዳዳሪዎች ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አሕመድ ሽዴ የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ ገዢዎች የንግድ የጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር በአወያይነት መርተዋል። ውይይቱ በዘላቂ ትስስር እና መሰረተ ልማት ላይ ያተኮረ ነው። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #Ethiopia #ኢትዮጵያ
የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ የዶሮ እርባታ ፕሮጀክት የ50 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ያደርጋል-የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አዴሲና
Jun 30, 2025 50
አዲስ አበባ ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ልማት ባንክ የሌማት ትሩፋት አካል ለሆነው የኢትዮጵያ የዶሮ እርባታ ፕሮጀክት የ50 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑን የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አዴሲና ገለጹ። ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ ዛሬ በስፔን ሲቪያ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) የተመራ ልዑካን ቡድን ኢትዮጵያን ወክሎ በኮንፍረንሱ ላይ እየተሳተፈ ነው። “Global Alliance Against Poverty and Hunger” ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን ያዘጋጀው ስብሰባ ተካሄዷል። የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሌማት ትሩፋት ዙሪያ ያላት ልምድ እንደ ተምሳሌታዊ ፕሮጀክት በስብሰባው ላይ አቅርበዋል። በተጨማሪ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የምታደርጋቸውን ሌሎች ሰፋፊ ጥረቶች አስመልክቶ ያላትን ተሞክሮም አጋርተዋል። ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል። ኢኒሼቲቩ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ሀገር በቀል ሀሳቦችን እና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ መሆኑን አመልክተዋል። በመንግስት እና በህዝቡ በባለቤትነት የተያዘ መሆኑ፣ድህነትን በመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አንጻር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ተናግረዋል። በተጨማሪም ኢኒሼቲቭ በሀገር ውስጥ ሀብት ላይ በመመስረት የሚተገበር መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ለምታደርጋቸው ትብብሮች ለኢኒሼቲቩ ድጋፍ በማፈላለግ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና ሊኖረው ይችላል ነው ያሉት ሚኒስትሩ። አክለውም ኢኒሼቲቩን በተጨማሪ ኢንቨስትመንት በስፋት መተግበር እንደሚቻል ገልጸው፥ ለዚህም የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ የተገበረው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎረም ለውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አመልክተዋል። በመጨረሻም ኢትዮጵያ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከሌሎች ሀገራት መልካም ተሞክሮ ለመማርም ዝግጁ ናት ብለዋል። የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አዴሲና በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት በሰራችው አመርቂ ስራ በስንዴ ምርት ሙሉ በሙሉ ራሷን መቻሏን ገልጸዋል። በትኩረት ተገቢው አመራር እና ድጋፍ ከተደረገ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንደሚቻል የኢትዮጵያ ስኬት እንደ ተጨባጭ ማሳያ ሊወሰድ እንደሚችል አመልክተዋል። ፕሬዝዳንቱ ባንኩ የኢትዮጵያ የሌማት ትሩፋት አካል የሆነውን የዶሮ እርባታ ፕሮጀክት 50 የሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለመደገፍ መወሰኑን ይፋ አድርገዋል። ኮንፍረንሱ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል። የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን በሚኖሩ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ ተሳትፎ ያደርጋል።
በፍትሐ ብሄር ክርክር ወቅት የተቋማት አመራሮች አስፈላጊ መረጃዎችን አደራጅቶ የማቅረብ ልምድና በቂ ግንዛቤ ሊያዳብሩ ይገባል
Jun 30, 2025 47
ባህርዳር ፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ) ፡-በፍትሐ ብሄር ክርክር ወቅት የተቋማት አመራሮች አስፈላጊ መረጃዎችን አደራጅቶ የማቅረብ ልምድና በቂ ግንዛቤ ሊያዳብሩ እንደሚገባ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ። መንግስት ተከራካሪ በሆነባቸው የፍትሃ ብሄር ጉዳዮች በሚያጋጥሙ ችግሮችና መፍትሄዎች፤ የክልሉ ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅና የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ በባህር ዳር እየተካሄደ ይገኛል። የመድረኩ ዓላማ የመንግስት ተቋማት የፍትሃ ብሄር ክርክር ሲያጋጥማቸው በጉዳዩ ላይ የተሟላ ዝግጅት በማድረግና አስፈላጊ መረጃዎችን ለፍርድ ቤቶች በማቅረብ የህዝብና የመንግስት ንብረቶችን ለመጠበቅ መሆኑም ታውቋል። በዚሁ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አለምአንተ አግደው፤ የመንግሥት ተቋማት የፍትሃ ብሄር ክርክር ሲያጋጥማቸው የሚስተዋሉ ክፍተቶች እየተበራከቱ መሆኑን አንስተዋል። የፍርድ ቤቶች ሚና ነፃ የዳኝነት አገልግሎት መስጠት መሆኑን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ፤ በክርክር ሂደት ከሚዛናቸው በመጉደል በተቋማት አሰራሮች የሚታዩ ክፍተቶችን ሊሸፍኑ የማይችሉ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህ ረገድ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ተቋማት አመራሮች ኃላፊነት ያለባቸው መሆኑን ገልጸው ይህ ሲባል ግን ፍርድ ቤቶች የመንግሥትና የሕዝብ ጥቅም በሚጎዳበት አጋጣሚ በዝምታ ይመለከታሉ ማለት አይደለም ብለዋል። በመሆኑም የመንግሥት ተቋማት የተቋሞቻቸውን ጉዳዮች በአግባቡ መምራትና የፍትሐ ብሔር ክርክር ሲያጋጥም አስፈላጊ ማስረጃዎችን በማቅረብ የህዝብን ሃብትና ንብረት መጠበቅና ማስከበር እንዳለባቸው አንስተዋል። የክልሉ መሬት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሰይፉ የሱፍ፤ በመንግስት የተያዙ የፍትሃ ብሄር ክሶች በአግባቡ ክርክር ስለማይደረግባቸው ከፍተኛ ሃብት እየታጣ መሆኑን ገልጸዋል። በፍርድ ቤቶች ከሚካሄዱ ክርክሮች በአብዛኛው መሬትና መሬት ነክ ጉዳዮች መሆናቸውን አንስተው ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ህግ አውጭውና ህግ ተርጓሚው ከአስፈፃሚው ጋር ተቀራርቦ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በምክክር መድረኩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የሚመለከታቸው አካላት እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎች እየተሳተፉ ነው።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የሦስት አገራት አምባሳደሮችን አሰናበቱ
Jun 30, 2025 87
አዲስ አበባ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በኢትዮጵያ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የካናዳ፣የስዊዲንና የሳኡዲ አረቢያ አምባሳደሮችን አሰናበቱ። ፕሬዝዳንቱ ያሰናበቱት የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ፣የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክና የሳኢዲ አረቢያ አምባሳደር ፋሃድ አልሁማያዳኒ (ዶ/ር) ናቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ ሦስቱም አምባሳደሮቹ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከአገራቱ ጋር በተለያዩ መስኮች የሁለትዮሽ ግንኙነትና ትብብር እንዲጠናከር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። በተለይም የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲሳለጥ እንዲሁም በሌሎች የልማት የትብብር ዘርፎች ግንኙነቱ እንዲጠናከር ላደረጉት አስተዋጽዖም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አምባሳደሮቹ በሌሎች መስኮች ለአብነትም በመልሶ ማልማት ሥራዎች ጉልህ አስተዋጽኦ መደረጉን አንስተው፥ትብብሮች በቀጣይም ሊጠናከር እንደሚገባ ጠይቀዋል። በቀጣይ በተለይም ውጤታማ የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቶች ይበልጥ ሊጠናከሩ እንደሚገባ ጥሪ ማቅረባቸውን ውይይቱን የተከታተሉት የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አምባሳደር ትዝታ ሙሉጌታ ለኢዜአ ገልጸዋል። አምባሳደሮቹ በበኩላቸው፥ በኢትዮጵያ ቆይታቸው አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር በርካታ ሥራዎች መሥራታቸውንና በዚህም አመርቂ ውጤት መገኙቱን ጠቅሰዋል። የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ በቆይታቸው የካናዳና ኢትዮጵያን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማስፋት የሚያስችሉ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። በተመሳሳይ የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ በቆይታቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ቅድሚያ በሰጠባቸው መስኮች ትብብር በማድረግ አበረታች ሥራዎች ማከናወናቸውን አስረድተዋል። አምባሳደሮቹ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች እየተዘመገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውንና መሰል ሥራዎችን ሊያጠናክር እንደሚገባ ተናግረዋል። በቀጣይም ግንኙነቱ ይበልጥ እንዲጠናከር የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
ፖለቲካ
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የሦስት አገራት አምባሳደሮችን አሰናበቱ
Jun 30, 2025 87
አዲስ አበባ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በኢትዮጵያ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የካናዳ፣የስዊዲንና የሳኡዲ አረቢያ አምባሳደሮችን አሰናበቱ። ፕሬዝዳንቱ ያሰናበቱት የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ፣የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክና የሳኢዲ አረቢያ አምባሳደር ፋሃድ አልሁማያዳኒ (ዶ/ር) ናቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ ሦስቱም አምባሳደሮቹ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከአገራቱ ጋር በተለያዩ መስኮች የሁለትዮሽ ግንኙነትና ትብብር እንዲጠናከር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። በተለይም የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲሳለጥ እንዲሁም በሌሎች የልማት የትብብር ዘርፎች ግንኙነቱ እንዲጠናከር ላደረጉት አስተዋጽዖም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አምባሳደሮቹ በሌሎች መስኮች ለአብነትም በመልሶ ማልማት ሥራዎች ጉልህ አስተዋጽኦ መደረጉን አንስተው፥ትብብሮች በቀጣይም ሊጠናከር እንደሚገባ ጠይቀዋል። በቀጣይ በተለይም ውጤታማ የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቶች ይበልጥ ሊጠናከሩ እንደሚገባ ጥሪ ማቅረባቸውን ውይይቱን የተከታተሉት የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አምባሳደር ትዝታ ሙሉጌታ ለኢዜአ ገልጸዋል። አምባሳደሮቹ በበኩላቸው፥ በኢትዮጵያ ቆይታቸው አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር በርካታ ሥራዎች መሥራታቸውንና በዚህም አመርቂ ውጤት መገኙቱን ጠቅሰዋል። የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ በቆይታቸው የካናዳና ኢትዮጵያን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማስፋት የሚያስችሉ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። በተመሳሳይ የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ በቆይታቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ቅድሚያ በሰጠባቸው መስኮች ትብብር በማድረግ አበረታች ሥራዎች ማከናወናቸውን አስረድተዋል። አምባሳደሮቹ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች እየተዘመገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውንና መሰል ሥራዎችን ሊያጠናክር እንደሚገባ ተናግረዋል። በቀጣይም ግንኙነቱ ይበልጥ እንዲጠናከር የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ(IAEA) ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ
Jun 30, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከአለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ(IAEA) ዋና ዳይሬክተር ማሪያኖ ግሮሲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ ጠዋት በሬይስ ኦፍ ሆፕ ጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ከመጡት የአለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ(IAEA) ዋና ዳይሬክተር ማሪያኖ ግሮሲ ጋር ተገናኝተናል ብለዋል። የአለም አቀፉ አቶሚክ ኃይል በኢትዮጵያ የሚያደርገው ድጋፍ በካንሰር ሕክምና ክብካቤ፣ የእንስሳት ጤና፣ የፀፀ ፍላይ ዝንብ ማጥፊያ፣ በኒኩለር ኢንጂነሪንግ እና የቁጥጥር ማዕቀፎች ላይ ያተኮረ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ውይይታችን በመካሄድ ላይ ባሉ ድጋፎች እና የወደፊት የትብብር እድሎች ላይ ያተኮረ ነበር ሲሉም አስታውቀዋል።
በቀበሌ ደረጃ መንግስታዊ አገልግሎት ተደራሽ መደረጉ ቀልጣፋ አገልግሎት ከማስገኘቱ ባለፈ የልማት ተሳታፊነታችንን እያሳደገ ነው -ነዋሪዎች
Jun 30, 2025 72
ጭሮ ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በቀበሌ ደረጃ መንግስታዊ አገልግሎት ተደራሽ በመደረጉ ለአስተዳደራዊ ጉዳዮቻቸው ፈጣን ምላሽ ከማስገኘቱ ባለፈ የልማት ተሳታፊነታቸው እያደገ መምጣቱን የዞኑ ዶባ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። በዞኑ በአዲስ መልክ ለተዘረጋው የቀበሌ አስተዳደር አገልግሎት መስጫ የሚውሉ ጽህፈት ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ ነው። ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት ለህብረተሰቡ ቅርብ የሆኑ የቀበሌ መዋቅሮች ከዚህ ቀደም ትኩረት በማጣታቸው አገልግሎት ፍለጋ እስከ ወረዳ ማዕከላት ሲመላለሱ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት የቀበሌ ፅህፈት ቤቶች በዘመናዊ መልኩ ተገንብተው ሙሉ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን የተናገሩት በወረዳው የባቱ ቀበሌ ነዋሪ ኢብራሂም ሁሴን ናቸው። በጤና፣ በትምህርት፣ በግብርና እና መሰል ጉዳዮች አገልግሎት ፍለጋ እስከ ወረዳ ማዕከል ድረስ ሲመላለሱ እንደነበር ያነሱት አስተያየት ሰጪው አሁን ላይ እነዚህን አገልግሎቶች በአካባቢያቸው በሚገኝ ቀበሌ ጽህፈት ቤት በቅርበት አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል። ከዚህ ቀደም በወረዳ ደረጃ ብቻ የሚያገኙትን የመሬት ነክ እና ግብርና አገልግሎቶችን በቀበሌ ማግኘታቸው የልማት ተሳታፊነታቸውን እያሳደገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አህመድ ኢብሮ ናቸው። ይህም የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን በማቃለል በአካባቢያቸው በሚከናወኑ የልማት ስራዎች ውስጥ ተሳትፏቸው እንዲጨምር ማድረጉንም ተናግረዋል። በብልጽግና ፓርቲ የዶባ ወረዳ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሙዘይን ከማል እንዳሉት በወረዳው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ በተጀመረው የቀበሌ አገልግሎት ማጠናከር ስራ ህብረተሰቡ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረግ ተችሏል። ሙሉ አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ በቅርበት እንዲሰጡ በመደረጉም አርሶ አደሩ ከግብርና ስራው እንዳይስተጓጎል ሁሉንም መንግስታዊ አገልግሎት በቅርበት እንዲያገኝ ማድረጉን ተናግረዋል። በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በሚገኙ 15 ወረዳዎችና አምስት ከተሞች የቀበሌ አደረጃጀቶችን በማጠናከር 3 ሺህ 522 ባለሙያዎች ተመድበው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ኢክራም ጠሀ ናቸው። በዚህም 512 የቀበሌ ፅህፈት ቤቶች በዘመናዊ መልኩ እንዲገነቡ መደረጉን አመልክተዋል።
መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደ ትናንቱ በትጋት ይሠራል - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Jun 29, 2025 180
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደ ትናንቱ በትጋት እንደሚሰራ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የአማራ ክልል ሕዝብ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መክፈል የማይገባውን ውድ ዋጋ በጥቂት ጥቅመኞች ምክንያት እየከፈለ መሆኑን ገልጿል። የፋኖን ታሪካዊ አነሣሥና ዓላማ ባልተከተለ አግባብ ራሳቸውን በፋኖ ስም የሚጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች በቀሰቀሱት ግጭትም የአማራ ክልል ሰላም እና ልማት ክፉኛ መጎዳቱን ጠቁሟል። መንግሥት ባለፉት ዓመታት ግጭቶችን ለማስወገድ በርካታ አማራጮችን ሲከተል መቆየቱ የሚታወስ ነው ያለው አገልግሎቱ ጥያቄ ያላቸዉ አካላትን በማቅረብ ለማነጋገር እና ለመደራደር በርካታ ጥረቶችን ማድረጉን ገልጿል ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- የአማራ ክልል ሕዝብ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መክፈል የማይገባዉን ውድ ዋጋ በጥቂት ጥቅመኞች ምክንያት እየከፈለ ይገኛል፡፡ የፋኖን ታሪካዊ አነሣሥ እና ዓላማ ባልተከተለ አግባብ ራሳቸዉን በፋኖ ስም የሚጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች በቀሰቀሱት ግጭት የአማራ ክልል ሰላም እና ልማት ክፉኛ ተጎድቷል፡፡ ፋኖ ሀገር በባዕድ ወራሪ እጅ በወደቀችበት እና ማእከላዊ መንግሥት በግዞት በቆየበት ወቅት ሀገርን ለማዳን የተደረገ ተጋድሎ የተመራበት ድንቅ ስያሜ ነው፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ግን የሀገሩን እና የክልሉን መንግሥት ለማፍረስ እና የባዕዳንን ተልእኮ ለማሳካት የተደራጁ ቡድኖች መጠሪያ ተደርጎ ሀገርን እና ሕዝብን ውድ ዋጋ አስከፍሏል፡፡ በሚሊዮኖች የሚቈጠሩ ታዳጊዎችን ከትምህርት ገበታ ነጥሏል፡፡ ሕዝብን ከልማት እንቅስቃሴዎች አሰናክሏል። የአማራ ክልል ሕዝብም የግጭት ጠማቂዎቹን እና የተላላኪዎቹን አጀንዳ በሚገባ ተገንዝቦ መንግሥት ሰላም እንዲያሰፍን በተደጋጋሚ ጥያቄዎችን በተለያዩ አግባቦች ሲያቀርብ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ የአማራ ክልል ሕዝብ ክልሉን ከግጭት እና ሥርዐት አልበኝነት ለማውጣት በየአካባቢዉ ተሰባስቦ ምክክር እና ውይይት አካሂዷል። የክልሉ ሕዝብ ጥያቄዎች በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን በአጀንዳነት እንዲያዙ አድርጓል፤ ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራዉ ቡድን ትክክለኛ የነፃነት ታጋይ መስሎት የተቀላቀለ ወጣት ወደ ሰላማዊ ሕይወቱ እንዲመለስ በሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ለምኗል፡፡ ከዚህም መሳ ለመሳ የፌደራል የፀጥታ ተቋማት እና የክልሉ የፀጥታ መዋቅር የክልሉን ሰላም ለማረጋጥ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፤ መሥዋዕትነትም ከፍለዋል፤ እየከፈሉም ነው፡፡ በዚህም በክልሉ አብዛኞቹ አካባቢዎች ሰላም ማስፈን ተችሏል፡፡ በተፈጠረው አስቻይ ሁኔታም የክልሉ ሕዝብ ከልማት ጥረቶች ወደ ኋላ እንዳይቀር በርካታ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል። ይሁን እንጅ በፀጥታ ኃይላችን ጥረት እና በሀገር ሽማግሌዎች ተማፅኖ አንጻራዊ ሰላም ቢሰፍንም ሕዝቡ በሚሻዉ ልክ የክልሉ ሰላም ሙሉ ለሙሉ አልተረጋገጠም፤ የዜጎች እንቅስቃሴ ከእገታና ዘረፋ ስጋት በምልዓት አልተላቀቀም፡፡ የነገ ሀገር ተረካቢዎች በተሟላ መልኩ ወደ ትምህርት ገበታ አልተመለሱም፡፡ የልማት እንቅስቀሴዎች ሕዝብ እና መንግሥት በሚሹት ልክ እንዲፋጠኑ ምቹ ድባብ አልሰፈነም፡፡ በዚህ ምክንያት ሕዝቡ ብሶቱን ለመንግሥት ጎላ አድርጎ ለማሰማት በተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን አካሂዷል፡፡ በሰላማዊ ሰልፎቹ መንግሥት የክልሉን ሰላም በማረጋገጥ ልማትን እንዲያጠናክር ሕዝቡ ጠይቋል፡፡ መንግሥት የውስጥ ባንዳዎችን እና የውጭ ኃይሎችን አደብ እንዲያስገዛለት፣ ልጆቹ ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱለት፣ ማሳውን ወደ መጎልጎልና ማረስ እንዲሰማራ፣ በኑሮው በሰላም ወጥቶ መግባት እንዲችል ምቹ ድባብ እንዲፈጠርለት፣ ሰላሙን በጋራ ለመጠበቅ እንደተዘጋጀ እና መንግሥት ሕግ ለማስከበር የጀመረዉን ጥረት በፅናት እንደሚደግፍ በሰላማዊ ሰልፎቹ ገልጿል፡፡ መንግሥት ባለፉት ዓመታት ግጭቶችን ለማስወገድ በርካታ አማራጮችን ሲከተል መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ ጥያቄ ያላቸዉ አካላትን በማቅረብ ለማነጋገር እና ለመደራደር በርካታ ጥረቶችን አድርጓል፡፡ በተደጋጋሚ የይቅርታ እና ምሕረት ጥሪዎችን አቅርቧል፡፡ በዚህም በርካታ በስሕተት የጥፋት ኃይሎችን ተቀላቅለዉ የነበሩ አካላት እጃቸዉን በመስጠት ሕይወታቸዉን አትርፈዋል፤ ሕዝቡን ለመካስ የሚያስችል የተሐድሶ ሥልጠናም አግኝተዋል፡፡ ነገር ግን አሁንም ጥቂት ጥቅመኞች የሕዝቡን ሰላም እያወኩ የባዕዳንን ተልእኮ ለማሳካት እየተወራጩ ይገኛሉ፡፡ መንግሥት የሕዝቡን የሰላም፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደትናንቱ ዝግጁ ነው፤ መንግሥታዊ ኃላፊነቱም ነው፡፡ የአማራ ክልል ሕዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ ከክልሉ ሕዝብ፣ ከክልሉ አስተዳደር እና የፀጥታ ኃይል ጋር በመቀናጀት መንግሥት የላቀ ጥረት ያደርጋል፡፡ ሕዝቡ ከመንግሥት ጋር በመቀናጀት ሰላሙን ለመጠበቅ ያሳየዉን ቁርጠኝነትም ያደንቃል፡፡ የሰላም በሮችን ዛሬም ክፍት አድርጎ እየጠበቀ የሕዝቡን የሰላም እና የልማት ጥያቄ ለመመለስ ከመቼዉም ጊዜ በላቀ ደረጃ ዝግጁ መኾኑንም መንግሥት ያረጋግጣል፡፡ የሰላም አማራጮችን የማይቀበሉ አካላትን በክልሉ የፀጥታ መዋቅር እና በፌደራል መዋቅር አማካኝነት አደብ በማስገዛት የሕዝቡን ሰላም ለማረጋገጥ ይሠራል፡፡ ሕዝቡ በአደባባይ ያቀረባቸዉን ጥያቄዎች ከሕዝብ ጋር ለመመለስ ያላሰለሰ ጥረት ያደርጋል፡፡ ሕዝቡ በሠለጠነ አግባብ ሐሳቡን በመግለጹም መንግሥት ምስጋና ያቀርባል፡፡ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
መንግስት ህግ በማስከበር ሰላምና ልማትን ለማጽናት እያደረገ ላለው ጥረት ተሳትፏችንን እናጠናክራለን
Jun 29, 2025 115
ደብረ ብርሃን፣ደብረ ማርቆስ፣ገንዳ ውሃና ወልዲያ፤ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦መንግስት ህግ በማስከበር ሰላምና ልማትን ለማጽናት እያደረገ ላለው ጥረት ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎች ገለጹ። በክልሉ ደብረ ብርሃን፣ደብረ ማርቆስ፣ መተማ ዮሐንስ እና ወልዲያ ከተሞች ሰላምን የሚደግፉና ጽንፈኝነትን የሚያወግዙ ህዝባዊ ሰልፎች ዛሬ ተካሂደዋል። በደብረ ብርሃን ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ሰልፍ የተሳተፉት አቶ ከፍያለው ግርማ በሰጡት አስተያየት የሰላም እጦት ችግር በውይይትና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ታጥቀው በጫካ ያሉ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ወደሰላም እንዲመጡና የሰላም ፍላጎታቸውን ለማሰማት በሰልፉ መታደማቸውን ተናግረዋል። ኑሮውን ሎተሪ አዙሮ በመሸጥ የሚመራው ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ በፍቃዱ በለጠ በበኩሉ፥ሰርቶ ለማደግና ለመለወጥ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ገልጾ፣ ሰላም እንደሚፈልግ በጋራ ድምጹን ለማሰማት በሰልፉ መሳተፉን ገልጿል። የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የሰላም እጦት ችግሩን ለመፍታት መንግስት ህግ ከማስከበር ጎን ለጎን ለታጠቁ አካላት በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ማቅረቡን አስታውሰዋል። የጥፋት ሀይሎች በህዝብና በሀገር ላይ እየፈጸሙት ያለውን የጥፋት ተግባር በማቆም የህዝብን ጽኑ የሰላም ፍላጎት በማክበር የመንግስትን የሰላም አማራጭ ሊቀበሉ ይገባል ብለዋል። በተያያዘ ዜና በደብረ ማረቆስ ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ሰልፍ ላይ የተሳተፉት ወይዘሮ እታገኝ አዳነ፥ ባለፉት ሁለት ዓመታት ያሳለፍነው ችግር እንዲያበቃ እንፈልጋለን፤ የእኛ ፍላጎት ዘላቂ ሰላምና ልማት ነው ብለዋል። ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም እንዲመጡ እንፈልጋለን ያሉት ወይዘሮ እታገኝ፣ ለአካባቢው ሰላም መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ሌላዋ ተሳታፊ ወይዘሮ አንለይ ተረፈ በበኩላቸው፥ ሰው በሰላም ወጥቶ መግባትና ሰርቶ መብላት የሚችለው ሰላም ሲኖር ነው ብለዋል። ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ በላይ እንየው በበኩላቸው፥ በግጭት ሰቆቃ፣ መከራና ስቃይ እንጂ የሚመጣ ለውጥ የለም ፤ ሰላምን እንደምንፈልግ በይፋ ለመግለጽ ዛሬ በሰልፉ ላይ ተገኝተናል ብሏል። አንድነታችንን በማጠናከር ሰላምና ልማትን ማጽናት የትኩረት አቅጣጫችን ነው ያሉት ደግሞ የደብረ ማርቆስ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ ናቸው። "ህዝቡ ለሰላሙ ያሳየውን ቁርጠኝነት በማስቀጠል በከተማው የተጀመረው የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ፣የኮሪደር ልማትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እናበቃለን ብለዋል። የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ በበኩላቸው፥ ህብረተሰቡ በተባበረ ድምጽ ጽንፈኞች ከጥፋት ተግባራቸው እንዲታቀቡ ያሳየው ቁርጠኝነት ትልቅ አቅም ነው ብለዋል። በሌላ በኩል በመተማ ዮሐንስ ከተማ በተካሄደ ሰልፍ የተሳተፉት አቶ ጥላሁን ንጉሴ በበኩላቸው፥በአካባቢው ጸጥታ ችግር ምክንያት ህዝቡ በሰላም ወጥቶ መግባት ቀርቶ የተሻለ ህክምና እንኳ ለማግኘት ተቸግሮ እንደነበር አስታውሰዋል። መንግስት የጀመረውን የህግ የማስከበር ሥራ እንደሚደግፉ ገልጸው፣ በጫካ ያለው ሃይል የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበልና ሰላምን እንደምንፈልግ መልዕክት ለማስተላለፋ ሰልፍ መውጣታቸውን ተናግረዋል። ሌላኛዋ የሰልፉ ተሳታፊ ወይዘሮ ሲሳይነሽ ይርጋ በበኩላቸው፥ ፅንፈኝነት የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን ጭምር ሰለባ እያደረገ በመሆኑ ከመንግስት ጎን ሆነው ለመታገል ቁርጠኛ መሆናቸውን ነው የገለጹት። ጽንፈኝነትን ማውገዝ ብቻ ሳይሆን መታገልም ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የመተማ ዮሐንስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሀብቴ አዲሱ ናቸው። መንግስት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ልማትን ለማረጋገጥ የጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ህዝቡ ከመንግስት ጎን ሆኖ የሚያደርገውን አስተዋጾ እንዲያጠናክርም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ በወልዲያ ከተማ በተካሄደ ሰልፍ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሰላም እጦት ያተረፉት የሰዎች ሞት፣ እገታ፣ ዝርፊያና ስደትን ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። መንግስት ሰላም እንዲጠናከር ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች ወደሰላም እንዲመጡ ያቀረበውን ጥሪ እንደሚደግፉ ገልጸው፣ የጥፋት ሀይሎች ጥሪውን በመቀበል ወደሰላም እንዲመጡ ጠይቀዋል። የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፥የጽንፈኞች እኩይ ሴራ የልማት ሥራን እንዳያደናቅፍ ጠንክሮ መታገል ይገባል ብለዋል። የታጠቁ ሃይሎችም የህዝብን ድምጽ በመስማትና በማክበር መንግስት በተደጋጋሚ ያቀረበውን የሰላም አማረጭ ተቀብለው ህዝባቸውን እንዲክሱም ከንቲባው አስገንዝበዋል። በተለያዩ ከተሞች በተካሄዱ ህዝባዊ ሰልፎች ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለሰላም ጽኑ ፍላጎት እንዳላቸውና ጽንፈኝነት ሀገርና ህዝብን ስለሚጎዳ ለሰላማቸው ከመንግስት ጎን እንደሚቆሙ ገልጸዋል።
ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እና ልማት እንዲፋጠን ድጋፋችንን እናጠናክራለን
Jun 29, 2025 121
ባህርዳር፤ ሰኔ 22/2017 (ኢዜአ) በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እና የልማት ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በባህርዳር ከተማ የህዝባዊ ሰልፍ ተሳታፊዎች ገለጹ። በባህርዳር ከተማ ‘‘ሀገርን ለማፅናት እና ለማበልፀግ ከመንግስት ጎን እንሰለፋለን’’ በሚል መሪ ሀሳብ ሰላምን የሚደግፍ ህዝባዊ ሰልፍ ዛሬ ተካሂዷል። ከሰልፉ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ትዕዛዙ ገብረኢየሱስ ለኢዜአ እንደገለጸው በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ ለህዝቡ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው። በክልሉ አሁን ላይ ባለው ሰላም በከተማው ልማት እንዲፋጠንና የወጣቶች ተጠቃሚነት እያደገ እንዲመጣ ማስቻሉን ገልጿል። የተገኘው ሰላም ዘላቂ እንዲሆንና የልማት ስራዎች እንዲጠናከሩ ተሳትፏችንን እናጠናክራለን " ያለው ወጣት ትዕዛዙ የታጠቁ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም እንዲመጡ ጠይቋል ። "የሰላም እጦት የሚያስከትለው ጥፋት በመሆኑ ለሰላም ዘብ ለመቆም ቆርጠን ተነስተናል" ያሉት ደግሞ የሰልፉ ታዳሚ ወይዘሮ አስረሱ ጌትነት ናቸው። በከተማው አሁን ላይ ባለው ሰላም ተስፋ ሰጭ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን ተናግረዋል። "በጫካ ላሉ የታጠቁ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላም ሊመጡ ይገባል" ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል። ‘‘በክልላችን ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ ድምፃችንን ለማሰማት በሰልፉ ተሳትፈናል ’’ ያለው ደግሞ ወጣት ሳለአምላክ አድማሱ ነው። ሰላም ለአንድ ወገን የሚተው አለመሆኑን ጠቁሞ "ሁላችንም ከመንግስት ጎን በመሰለፍ ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ልማት እንዲረጋገጥ በቁርጠኝነት ልንሰራ ይገባል" ብሏል። የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው የከተማው አስተዳደር ሰላምን በማጽናት ልማትን ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። "ፅንፈኛው ኃይል በክልሉና በከተማችን ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት አድርሷል" ያሉት አቶ ጎሹ ህፃናት ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ ማድረጉን ጠቅሰዋል። የፅንፈኛው ሀይል የክልሉን ልማትና ዕድገት ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ህብረተሰቡ በዛሬው ሰልፍ ጽንፈኝነትን በማውገዝ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የደገፈበት መሆኑን ተናግረዋል ። ጫካ የሚገኙ ኃይሎች የሰላም ጥሪን ተቀብለው ህዝባቸውን እንዲክሱም አሳስበዋል። በከተማው ሰላምን ዘላቂ ለማድረግና ልማትን ለማፋጠን እየተደረገ ባለው ጥረት የህብረተሰቡ ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ይኽው የህዝቡ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል ። በሰልፉ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
የመንግስትን የልማት እቅዶች በመደገፍ እና የሰላም ጥረቶች በማገዝ የድርሻችንን እንወጣለን
Jun 29, 2025 108
ደሴ፤ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስትን የልማት እቅዶች በመደገፍና የሰላም ጥረቶች በማገዝ የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ በደሴ ከተማ በተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎች ተናገሩ። በደሴ ከተማና አካባቢው ሰላምና ልማትን የሚደግፍና ፅንፈኝነትን የሚያወግዝ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሃዷል። ከሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ዘሪሁን ማንደፍሮ፣ ወይዘሮ መብራት ፈለቀ እና አቶ ሰለሞን አሰፋ፤ ከምንም በላይ ሰላምና ልማታችንን አጥብቀን እንሻለን ጸረ ሰላም ቡድኖችን ደግሞ እናወግዛለን ብለዋል። የደሴና አካባቢው ሰላም አስተማማኝ የሆነው በህዝቡ ትብብርና ጥረት፣ በፀጥታ አካላት ትጋት መሆኑን አንስተው ይህንኑ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ተናግረዋል። በመሆኑም የመንግስትን የልማት እቅዶችን በመደገፍና የሰላም ጥረቶችን በማገዝ የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የመንግስት የሰላምና የልማት ጥረት የሚደገፍ በመሆኑ ለሰላማዊ ሰልፍ መውጣታቸውን ተናግረው ለእኩይ ዓላማ የሚንቀሳቀሱ አካላት ከድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባም አንስተዋል። በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በህዝብ ስም እየማሉ ግድያ፣ ዘረፋ፣ እገታና ውንብድና የሚፈጽሙ ጽንፈኞችን በፅኑ እናወግዛለን፤ ለሰላማችንም ዘብ እንቆማለን ሲሉ ተናግረዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ፤ በሁሉም አካባቢዎች ህብረተሰቡ አንድነቱን በማጠናከር እያሳየ ያለውን ሁለንተናዊ ድጋፍና ተሳትፎ አድንቀዋል። ከውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በማበር ሀገርን ለማፍረስ የሚሰሩ ቡድኖች ከክህደት እና ሸፍጥ በመውጣት ለሀገር ልማትና እድገት በጋራ እንዲቆሙም ጠይቀዋል። የተጀመሩ ሀገራዊ የልማት እቅዶችን ከዳር በማድረስ ሀገራዊ ህብረ ብሄራዊ አንድነትና ሰላምን በማፅናት ሀገር መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል። በዛሬው እለት ከደሴ ከተማ በተጨማሪ በኮምቦልቻ፣ ሐይቅ እና ሌሎችም ከተሞች ተመሳሳይ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፎች ተካሂደዋል።
ሰላማችንን በማጽናት በከተማችን የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እንዲበቁ የድርሻችንን ለማበርከት ዝግጁ ነን
Jun 29, 2025 109
ጎንደር ፤ሰኔ 22/2017 (ኢዜአ) ሰላማችንን በማጽናት በከተማችን የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የድርሻችንን ለማበርከት ዝግጁ ነን ሲሉ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ሰላምን የሚደግፍና ጽንፈኝነትን የሚያወግዝ ህዝባዊ ሰልፍ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል፡፡ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ነዋሪዎች እንደተናገሩት ጎንደር በከፍተኛ የልማት ሥራ ላይ ትገኛለች፤ ሰላሙንና ልማቱን ለማስቀጠል ደግሞ እኛ ነዋሪዎች ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኞች ነን ሲሉ ተናግረዋል "ጎንደር የቀደመ ገናና ስሟንና ታሪኳን የሚመጥን የመልማት እድል ያገኘችው አሁን ነው" ያሉት በህዝባዊ ሰልፉ ላይ የተሳተፉት አቶ ጌትነት መንግስቱ ናቸው፡፡ ከተማዋ ያገኘችው ዘርፈ ብዙ የልማት እድሎች ለህዝቡ የዘመናት የልማት ጥያቄ መሰረታዊ ምላሽ የሚሰጡ በመሆናቸው ለሰላም ዘብ በመቆም ልማቱን ለማስቀጠል የድርሻቸውን ለማበርከት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ሌላዋ የሰልፉ ተሳታፊ ወይዘሮ አለምነሽ ብርሃኑ በበኩላቸው በከተማው እየተካሄዱ የሚገኙ የኮሪደር ልማትና የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ሥራዎች ታሪካችንን ያደሱ አኩሪ የልማት ተግባራት ናቸው ብለዋል፡፡ "ጎንደር በአሁኑ ወቅት ያገኘችው የልማት ዕድል በምንም መንገድ ወደኋላ ሊመለስና ሊቀለበስ የማይችል ነው" ያሉት ወይዘሮ አለምነሽ ለልማትና ለሰላም ጸር የሆነውን ጽንፈኝነት ለመታገል ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። በፌደራልና በክልሉ መንግስት ድጋፍ በከተማችን እየተካሄዱ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች በርካታ ወጣቶችን የሥራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ አስችሏል ያለው ደግሞ ወጣት መሃመድ አብዲ ነው፡፡ በለውጥና በአዲስ የእድገት ጎዳና ላይ የምትገኘው ሀገራችን ወጣቶች በሃገራቸው ብሩህ ተስፋ እንዲሰንቁና ለልማትና ሰላም ማስፈን እንዲተጉ መነሳሳት ፈጥሯል ብሏል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በጎንደር ከተማ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን አስታውሰዋል። የከተማው ህዝብ ከዳር አስከ ዳር በመነሳት የልማት ሥራዎችን በገንዘብ፣ በጉልበቱና በእውቀቱ እየደገፈ መሆኑን የጠቆሙት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው፣ "ጎንደር ለሰላም ዋጋ የምትሰጥ ከተማ ነች" ብለዋል፡፡ ለከተማዋ እድገት አስተዋጽኦ ላደረጉ የፌደራልና የክልሉ አመራሮች እንዲሁም በሀገር ውስጥና በውጭ ላሉ ወገኖችም ምስጋና አቅርበዋል። በህዝባዊ ሰልፉ ላይ የመንግስት ሠራተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ፖለቲካ
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የሦስት አገራት አምባሳደሮችን አሰናበቱ
Jun 30, 2025 87
አዲስ አበባ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በኢትዮጵያ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ የካናዳ፣የስዊዲንና የሳኡዲ አረቢያ አምባሳደሮችን አሰናበቱ። ፕሬዝዳንቱ ያሰናበቱት የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ፣የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክና የሳኢዲ አረቢያ አምባሳደር ፋሃድ አልሁማያዳኒ (ዶ/ር) ናቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ ሦስቱም አምባሳደሮቹ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከአገራቱ ጋር በተለያዩ መስኮች የሁለትዮሽ ግንኙነትና ትብብር እንዲጠናከር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። በተለይም የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲሳለጥ እንዲሁም በሌሎች የልማት የትብብር ዘርፎች ግንኙነቱ እንዲጠናከር ላደረጉት አስተዋጽዖም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አምባሳደሮቹ በሌሎች መስኮች ለአብነትም በመልሶ ማልማት ሥራዎች ጉልህ አስተዋጽኦ መደረጉን አንስተው፥ትብብሮች በቀጣይም ሊጠናከር እንደሚገባ ጠይቀዋል። በቀጣይ በተለይም ውጤታማ የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቶች ይበልጥ ሊጠናከሩ እንደሚገባ ጥሪ ማቅረባቸውን ውይይቱን የተከታተሉት የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አምባሳደር ትዝታ ሙሉጌታ ለኢዜአ ገልጸዋል። አምባሳደሮቹ በበኩላቸው፥ በኢትዮጵያ ቆይታቸው አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር በርካታ ሥራዎች መሥራታቸውንና በዚህም አመርቂ ውጤት መገኙቱን ጠቅሰዋል። የካናዳ አምባሳደር ጆሽዋ ታባህ በቆይታቸው የካናዳና ኢትዮጵያን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማስፋት የሚያስችሉ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። በተመሳሳይ የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ በቆይታቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ቅድሚያ በሰጠባቸው መስኮች ትብብር በማድረግ አበረታች ሥራዎች ማከናወናቸውን አስረድተዋል። አምባሳደሮቹ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች እየተዘመገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውንና መሰል ሥራዎችን ሊያጠናክር እንደሚገባ ተናግረዋል። በቀጣይም ግንኙነቱ ይበልጥ እንዲጠናከር የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ(IAEA) ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ
Jun 30, 2025 97
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከአለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ(IAEA) ዋና ዳይሬክተር ማሪያኖ ግሮሲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ ጠዋት በሬይስ ኦፍ ሆፕ ጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ከመጡት የአለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ(IAEA) ዋና ዳይሬክተር ማሪያኖ ግሮሲ ጋር ተገናኝተናል ብለዋል። የአለም አቀፉ አቶሚክ ኃይል በኢትዮጵያ የሚያደርገው ድጋፍ በካንሰር ሕክምና ክብካቤ፣ የእንስሳት ጤና፣ የፀፀ ፍላይ ዝንብ ማጥፊያ፣ በኒኩለር ኢንጂነሪንግ እና የቁጥጥር ማዕቀፎች ላይ ያተኮረ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ውይይታችን በመካሄድ ላይ ባሉ ድጋፎች እና የወደፊት የትብብር እድሎች ላይ ያተኮረ ነበር ሲሉም አስታውቀዋል።
በቀበሌ ደረጃ መንግስታዊ አገልግሎት ተደራሽ መደረጉ ቀልጣፋ አገልግሎት ከማስገኘቱ ባለፈ የልማት ተሳታፊነታችንን እያሳደገ ነው -ነዋሪዎች
Jun 30, 2025 72
ጭሮ ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በቀበሌ ደረጃ መንግስታዊ አገልግሎት ተደራሽ በመደረጉ ለአስተዳደራዊ ጉዳዮቻቸው ፈጣን ምላሽ ከማስገኘቱ ባለፈ የልማት ተሳታፊነታቸው እያደገ መምጣቱን የዞኑ ዶባ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። በዞኑ በአዲስ መልክ ለተዘረጋው የቀበሌ አስተዳደር አገልግሎት መስጫ የሚውሉ ጽህፈት ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ ነው። ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት ለህብረተሰቡ ቅርብ የሆኑ የቀበሌ መዋቅሮች ከዚህ ቀደም ትኩረት በማጣታቸው አገልግሎት ፍለጋ እስከ ወረዳ ማዕከላት ሲመላለሱ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት የቀበሌ ፅህፈት ቤቶች በዘመናዊ መልኩ ተገንብተው ሙሉ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን የተናገሩት በወረዳው የባቱ ቀበሌ ነዋሪ ኢብራሂም ሁሴን ናቸው። በጤና፣ በትምህርት፣ በግብርና እና መሰል ጉዳዮች አገልግሎት ፍለጋ እስከ ወረዳ ማዕከል ድረስ ሲመላለሱ እንደነበር ያነሱት አስተያየት ሰጪው አሁን ላይ እነዚህን አገልግሎቶች በአካባቢያቸው በሚገኝ ቀበሌ ጽህፈት ቤት በቅርበት አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል። ከዚህ ቀደም በወረዳ ደረጃ ብቻ የሚያገኙትን የመሬት ነክ እና ግብርና አገልግሎቶችን በቀበሌ ማግኘታቸው የልማት ተሳታፊነታቸውን እያሳደገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አህመድ ኢብሮ ናቸው። ይህም የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን በማቃለል በአካባቢያቸው በሚከናወኑ የልማት ስራዎች ውስጥ ተሳትፏቸው እንዲጨምር ማድረጉንም ተናግረዋል። በብልጽግና ፓርቲ የዶባ ወረዳ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሙዘይን ከማል እንዳሉት በወረዳው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ በተጀመረው የቀበሌ አገልግሎት ማጠናከር ስራ ህብረተሰቡ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረግ ተችሏል። ሙሉ አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ በቅርበት እንዲሰጡ በመደረጉም አርሶ አደሩ ከግብርና ስራው እንዳይስተጓጎል ሁሉንም መንግስታዊ አገልግሎት በቅርበት እንዲያገኝ ማድረጉን ተናግረዋል። በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በሚገኙ 15 ወረዳዎችና አምስት ከተሞች የቀበሌ አደረጃጀቶችን በማጠናከር 3 ሺህ 522 ባለሙያዎች ተመድበው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ኢክራም ጠሀ ናቸው። በዚህም 512 የቀበሌ ፅህፈት ቤቶች በዘመናዊ መልኩ እንዲገነቡ መደረጉን አመልክተዋል።
መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደ ትናንቱ በትጋት ይሠራል - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Jun 29, 2025 180
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደ ትናንቱ በትጋት እንደሚሰራ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የአማራ ክልል ሕዝብ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መክፈል የማይገባውን ውድ ዋጋ በጥቂት ጥቅመኞች ምክንያት እየከፈለ መሆኑን ገልጿል። የፋኖን ታሪካዊ አነሣሥና ዓላማ ባልተከተለ አግባብ ራሳቸውን በፋኖ ስም የሚጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች በቀሰቀሱት ግጭትም የአማራ ክልል ሰላም እና ልማት ክፉኛ መጎዳቱን ጠቁሟል። መንግሥት ባለፉት ዓመታት ግጭቶችን ለማስወገድ በርካታ አማራጮችን ሲከተል መቆየቱ የሚታወስ ነው ያለው አገልግሎቱ ጥያቄ ያላቸዉ አካላትን በማቅረብ ለማነጋገር እና ለመደራደር በርካታ ጥረቶችን ማድረጉን ገልጿል ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- የአማራ ክልል ሕዝብ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መክፈል የማይገባዉን ውድ ዋጋ በጥቂት ጥቅመኞች ምክንያት እየከፈለ ይገኛል፡፡ የፋኖን ታሪካዊ አነሣሥ እና ዓላማ ባልተከተለ አግባብ ራሳቸዉን በፋኖ ስም የሚጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች በቀሰቀሱት ግጭት የአማራ ክልል ሰላም እና ልማት ክፉኛ ተጎድቷል፡፡ ፋኖ ሀገር በባዕድ ወራሪ እጅ በወደቀችበት እና ማእከላዊ መንግሥት በግዞት በቆየበት ወቅት ሀገርን ለማዳን የተደረገ ተጋድሎ የተመራበት ድንቅ ስያሜ ነው፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ግን የሀገሩን እና የክልሉን መንግሥት ለማፍረስ እና የባዕዳንን ተልእኮ ለማሳካት የተደራጁ ቡድኖች መጠሪያ ተደርጎ ሀገርን እና ሕዝብን ውድ ዋጋ አስከፍሏል፡፡ በሚሊዮኖች የሚቈጠሩ ታዳጊዎችን ከትምህርት ገበታ ነጥሏል፡፡ ሕዝብን ከልማት እንቅስቃሴዎች አሰናክሏል። የአማራ ክልል ሕዝብም የግጭት ጠማቂዎቹን እና የተላላኪዎቹን አጀንዳ በሚገባ ተገንዝቦ መንግሥት ሰላም እንዲያሰፍን በተደጋጋሚ ጥያቄዎችን በተለያዩ አግባቦች ሲያቀርብ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ የአማራ ክልል ሕዝብ ክልሉን ከግጭት እና ሥርዐት አልበኝነት ለማውጣት በየአካባቢዉ ተሰባስቦ ምክክር እና ውይይት አካሂዷል። የክልሉ ሕዝብ ጥያቄዎች በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን በአጀንዳነት እንዲያዙ አድርጓል፤ ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራዉ ቡድን ትክክለኛ የነፃነት ታጋይ መስሎት የተቀላቀለ ወጣት ወደ ሰላማዊ ሕይወቱ እንዲመለስ በሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ለምኗል፡፡ ከዚህም መሳ ለመሳ የፌደራል የፀጥታ ተቋማት እና የክልሉ የፀጥታ መዋቅር የክልሉን ሰላም ለማረጋጥ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፤ መሥዋዕትነትም ከፍለዋል፤ እየከፈሉም ነው፡፡ በዚህም በክልሉ አብዛኞቹ አካባቢዎች ሰላም ማስፈን ተችሏል፡፡ በተፈጠረው አስቻይ ሁኔታም የክልሉ ሕዝብ ከልማት ጥረቶች ወደ ኋላ እንዳይቀር በርካታ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል። ይሁን እንጅ በፀጥታ ኃይላችን ጥረት እና በሀገር ሽማግሌዎች ተማፅኖ አንጻራዊ ሰላም ቢሰፍንም ሕዝቡ በሚሻዉ ልክ የክልሉ ሰላም ሙሉ ለሙሉ አልተረጋገጠም፤ የዜጎች እንቅስቃሴ ከእገታና ዘረፋ ስጋት በምልዓት አልተላቀቀም፡፡ የነገ ሀገር ተረካቢዎች በተሟላ መልኩ ወደ ትምህርት ገበታ አልተመለሱም፡፡ የልማት እንቅስቀሴዎች ሕዝብ እና መንግሥት በሚሹት ልክ እንዲፋጠኑ ምቹ ድባብ አልሰፈነም፡፡ በዚህ ምክንያት ሕዝቡ ብሶቱን ለመንግሥት ጎላ አድርጎ ለማሰማት በተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን አካሂዷል፡፡ በሰላማዊ ሰልፎቹ መንግሥት የክልሉን ሰላም በማረጋገጥ ልማትን እንዲያጠናክር ሕዝቡ ጠይቋል፡፡ መንግሥት የውስጥ ባንዳዎችን እና የውጭ ኃይሎችን አደብ እንዲያስገዛለት፣ ልጆቹ ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱለት፣ ማሳውን ወደ መጎልጎልና ማረስ እንዲሰማራ፣ በኑሮው በሰላም ወጥቶ መግባት እንዲችል ምቹ ድባብ እንዲፈጠርለት፣ ሰላሙን በጋራ ለመጠበቅ እንደተዘጋጀ እና መንግሥት ሕግ ለማስከበር የጀመረዉን ጥረት በፅናት እንደሚደግፍ በሰላማዊ ሰልፎቹ ገልጿል፡፡ መንግሥት ባለፉት ዓመታት ግጭቶችን ለማስወገድ በርካታ አማራጮችን ሲከተል መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ ጥያቄ ያላቸዉ አካላትን በማቅረብ ለማነጋገር እና ለመደራደር በርካታ ጥረቶችን አድርጓል፡፡ በተደጋጋሚ የይቅርታ እና ምሕረት ጥሪዎችን አቅርቧል፡፡ በዚህም በርካታ በስሕተት የጥፋት ኃይሎችን ተቀላቅለዉ የነበሩ አካላት እጃቸዉን በመስጠት ሕይወታቸዉን አትርፈዋል፤ ሕዝቡን ለመካስ የሚያስችል የተሐድሶ ሥልጠናም አግኝተዋል፡፡ ነገር ግን አሁንም ጥቂት ጥቅመኞች የሕዝቡን ሰላም እያወኩ የባዕዳንን ተልእኮ ለማሳካት እየተወራጩ ይገኛሉ፡፡ መንግሥት የሕዝቡን የሰላም፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደትናንቱ ዝግጁ ነው፤ መንግሥታዊ ኃላፊነቱም ነው፡፡ የአማራ ክልል ሕዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ ከክልሉ ሕዝብ፣ ከክልሉ አስተዳደር እና የፀጥታ ኃይል ጋር በመቀናጀት መንግሥት የላቀ ጥረት ያደርጋል፡፡ ሕዝቡ ከመንግሥት ጋር በመቀናጀት ሰላሙን ለመጠበቅ ያሳየዉን ቁርጠኝነትም ያደንቃል፡፡ የሰላም በሮችን ዛሬም ክፍት አድርጎ እየጠበቀ የሕዝቡን የሰላም እና የልማት ጥያቄ ለመመለስ ከመቼዉም ጊዜ በላቀ ደረጃ ዝግጁ መኾኑንም መንግሥት ያረጋግጣል፡፡ የሰላም አማራጮችን የማይቀበሉ አካላትን በክልሉ የፀጥታ መዋቅር እና በፌደራል መዋቅር አማካኝነት አደብ በማስገዛት የሕዝቡን ሰላም ለማረጋገጥ ይሠራል፡፡ ሕዝቡ በአደባባይ ያቀረባቸዉን ጥያቄዎች ከሕዝብ ጋር ለመመለስ ያላሰለሰ ጥረት ያደርጋል፡፡ ሕዝቡ በሠለጠነ አግባብ ሐሳቡን በመግለጹም መንግሥት ምስጋና ያቀርባል፡፡ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
መንግስት ህግ በማስከበር ሰላምና ልማትን ለማጽናት እያደረገ ላለው ጥረት ተሳትፏችንን እናጠናክራለን
Jun 29, 2025 115
ደብረ ብርሃን፣ደብረ ማርቆስ፣ገንዳ ውሃና ወልዲያ፤ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦መንግስት ህግ በማስከበር ሰላምና ልማትን ለማጽናት እያደረገ ላለው ጥረት ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎች ገለጹ። በክልሉ ደብረ ብርሃን፣ደብረ ማርቆስ፣ መተማ ዮሐንስ እና ወልዲያ ከተሞች ሰላምን የሚደግፉና ጽንፈኝነትን የሚያወግዙ ህዝባዊ ሰልፎች ዛሬ ተካሂደዋል። በደብረ ብርሃን ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ሰልፍ የተሳተፉት አቶ ከፍያለው ግርማ በሰጡት አስተያየት የሰላም እጦት ችግር በውይይትና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ታጥቀው በጫካ ያሉ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ወደሰላም እንዲመጡና የሰላም ፍላጎታቸውን ለማሰማት በሰልፉ መታደማቸውን ተናግረዋል። ኑሮውን ሎተሪ አዙሮ በመሸጥ የሚመራው ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ በፍቃዱ በለጠ በበኩሉ፥ሰርቶ ለማደግና ለመለወጥ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ገልጾ፣ ሰላም እንደሚፈልግ በጋራ ድምጹን ለማሰማት በሰልፉ መሳተፉን ገልጿል። የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የሰላም እጦት ችግሩን ለመፍታት መንግስት ህግ ከማስከበር ጎን ለጎን ለታጠቁ አካላት በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ማቅረቡን አስታውሰዋል። የጥፋት ሀይሎች በህዝብና በሀገር ላይ እየፈጸሙት ያለውን የጥፋት ተግባር በማቆም የህዝብን ጽኑ የሰላም ፍላጎት በማክበር የመንግስትን የሰላም አማራጭ ሊቀበሉ ይገባል ብለዋል። በተያያዘ ዜና በደብረ ማረቆስ ከተማ በተካሄደ ህዝባዊ ሰልፍ ላይ የተሳተፉት ወይዘሮ እታገኝ አዳነ፥ ባለፉት ሁለት ዓመታት ያሳለፍነው ችግር እንዲያበቃ እንፈልጋለን፤ የእኛ ፍላጎት ዘላቂ ሰላምና ልማት ነው ብለዋል። ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም እንዲመጡ እንፈልጋለን ያሉት ወይዘሮ እታገኝ፣ ለአካባቢው ሰላም መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ሌላዋ ተሳታፊ ወይዘሮ አንለይ ተረፈ በበኩላቸው፥ ሰው በሰላም ወጥቶ መግባትና ሰርቶ መብላት የሚችለው ሰላም ሲኖር ነው ብለዋል። ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ በላይ እንየው በበኩላቸው፥ በግጭት ሰቆቃ፣ መከራና ስቃይ እንጂ የሚመጣ ለውጥ የለም ፤ ሰላምን እንደምንፈልግ በይፋ ለመግለጽ ዛሬ በሰልፉ ላይ ተገኝተናል ብሏል። አንድነታችንን በማጠናከር ሰላምና ልማትን ማጽናት የትኩረት አቅጣጫችን ነው ያሉት ደግሞ የደብረ ማርቆስ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ ናቸው። "ህዝቡ ለሰላሙ ያሳየውን ቁርጠኝነት በማስቀጠል በከተማው የተጀመረው የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ፣የኮሪደር ልማትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እናበቃለን ብለዋል። የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ በበኩላቸው፥ ህብረተሰቡ በተባበረ ድምጽ ጽንፈኞች ከጥፋት ተግባራቸው እንዲታቀቡ ያሳየው ቁርጠኝነት ትልቅ አቅም ነው ብለዋል። በሌላ በኩል በመተማ ዮሐንስ ከተማ በተካሄደ ሰልፍ የተሳተፉት አቶ ጥላሁን ንጉሴ በበኩላቸው፥በአካባቢው ጸጥታ ችግር ምክንያት ህዝቡ በሰላም ወጥቶ መግባት ቀርቶ የተሻለ ህክምና እንኳ ለማግኘት ተቸግሮ እንደነበር አስታውሰዋል። መንግስት የጀመረውን የህግ የማስከበር ሥራ እንደሚደግፉ ገልጸው፣ በጫካ ያለው ሃይል የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበልና ሰላምን እንደምንፈልግ መልዕክት ለማስተላለፋ ሰልፍ መውጣታቸውን ተናግረዋል። ሌላኛዋ የሰልፉ ተሳታፊ ወይዘሮ ሲሳይነሽ ይርጋ በበኩላቸው፥ ፅንፈኝነት የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን ጭምር ሰለባ እያደረገ በመሆኑ ከመንግስት ጎን ሆነው ለመታገል ቁርጠኛ መሆናቸውን ነው የገለጹት። ጽንፈኝነትን ማውገዝ ብቻ ሳይሆን መታገልም ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የመተማ ዮሐንስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሀብቴ አዲሱ ናቸው። መንግስት ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ልማትን ለማረጋገጥ የጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ህዝቡ ከመንግስት ጎን ሆኖ የሚያደርገውን አስተዋጾ እንዲያጠናክርም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ በወልዲያ ከተማ በተካሄደ ሰልፍ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሰላም እጦት ያተረፉት የሰዎች ሞት፣ እገታ፣ ዝርፊያና ስደትን ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። መንግስት ሰላም እንዲጠናከር ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች ወደሰላም እንዲመጡ ያቀረበውን ጥሪ እንደሚደግፉ ገልጸው፣ የጥፋት ሀይሎች ጥሪውን በመቀበል ወደሰላም እንዲመጡ ጠይቀዋል። የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፥የጽንፈኞች እኩይ ሴራ የልማት ሥራን እንዳያደናቅፍ ጠንክሮ መታገል ይገባል ብለዋል። የታጠቁ ሃይሎችም የህዝብን ድምጽ በመስማትና በማክበር መንግስት በተደጋጋሚ ያቀረበውን የሰላም አማረጭ ተቀብለው ህዝባቸውን እንዲክሱም ከንቲባው አስገንዝበዋል። በተለያዩ ከተሞች በተካሄዱ ህዝባዊ ሰልፎች ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለሰላም ጽኑ ፍላጎት እንዳላቸውና ጽንፈኝነት ሀገርና ህዝብን ስለሚጎዳ ለሰላማቸው ከመንግስት ጎን እንደሚቆሙ ገልጸዋል።
ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እና ልማት እንዲፋጠን ድጋፋችንን እናጠናክራለን
Jun 29, 2025 121
ባህርዳር፤ ሰኔ 22/2017 (ኢዜአ) በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እና የልማት ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በባህርዳር ከተማ የህዝባዊ ሰልፍ ተሳታፊዎች ገለጹ። በባህርዳር ከተማ ‘‘ሀገርን ለማፅናት እና ለማበልፀግ ከመንግስት ጎን እንሰለፋለን’’ በሚል መሪ ሀሳብ ሰላምን የሚደግፍ ህዝባዊ ሰልፍ ዛሬ ተካሂዷል። ከሰልፉ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ትዕዛዙ ገብረኢየሱስ ለኢዜአ እንደገለጸው በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ ለህዝቡ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው። በክልሉ አሁን ላይ ባለው ሰላም በከተማው ልማት እንዲፋጠንና የወጣቶች ተጠቃሚነት እያደገ እንዲመጣ ማስቻሉን ገልጿል። የተገኘው ሰላም ዘላቂ እንዲሆንና የልማት ስራዎች እንዲጠናከሩ ተሳትፏችንን እናጠናክራለን " ያለው ወጣት ትዕዛዙ የታጠቁ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም እንዲመጡ ጠይቋል ። "የሰላም እጦት የሚያስከትለው ጥፋት በመሆኑ ለሰላም ዘብ ለመቆም ቆርጠን ተነስተናል" ያሉት ደግሞ የሰልፉ ታዳሚ ወይዘሮ አስረሱ ጌትነት ናቸው። በከተማው አሁን ላይ ባለው ሰላም ተስፋ ሰጭ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን ተናግረዋል። "በጫካ ላሉ የታጠቁ ሀይሎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላም ሊመጡ ይገባል" ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል። ‘‘በክልላችን ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ ድምፃችንን ለማሰማት በሰልፉ ተሳትፈናል ’’ ያለው ደግሞ ወጣት ሳለአምላክ አድማሱ ነው። ሰላም ለአንድ ወገን የሚተው አለመሆኑን ጠቁሞ "ሁላችንም ከመንግስት ጎን በመሰለፍ ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ልማት እንዲረጋገጥ በቁርጠኝነት ልንሰራ ይገባል" ብሏል። የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው የከተማው አስተዳደር ሰላምን በማጽናት ልማትን ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። "ፅንፈኛው ኃይል በክልሉና በከተማችን ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት አድርሷል" ያሉት አቶ ጎሹ ህፃናት ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ ማድረጉን ጠቅሰዋል። የፅንፈኛው ሀይል የክልሉን ልማትና ዕድገት ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ህብረተሰቡ በዛሬው ሰልፍ ጽንፈኝነትን በማውገዝ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የደገፈበት መሆኑን ተናግረዋል ። ጫካ የሚገኙ ኃይሎች የሰላም ጥሪን ተቀብለው ህዝባቸውን እንዲክሱም አሳስበዋል። በከተማው ሰላምን ዘላቂ ለማድረግና ልማትን ለማፋጠን እየተደረገ ባለው ጥረት የህብረተሰቡ ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ይኽው የህዝቡ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል ። በሰልፉ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
የመንግስትን የልማት እቅዶች በመደገፍ እና የሰላም ጥረቶች በማገዝ የድርሻችንን እንወጣለን
Jun 29, 2025 108
ደሴ፤ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስትን የልማት እቅዶች በመደገፍና የሰላም ጥረቶች በማገዝ የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ በደሴ ከተማ በተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎች ተናገሩ። በደሴ ከተማና አካባቢው ሰላምና ልማትን የሚደግፍና ፅንፈኝነትን የሚያወግዝ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሃዷል። ከሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ዘሪሁን ማንደፍሮ፣ ወይዘሮ መብራት ፈለቀ እና አቶ ሰለሞን አሰፋ፤ ከምንም በላይ ሰላምና ልማታችንን አጥብቀን እንሻለን ጸረ ሰላም ቡድኖችን ደግሞ እናወግዛለን ብለዋል። የደሴና አካባቢው ሰላም አስተማማኝ የሆነው በህዝቡ ትብብርና ጥረት፣ በፀጥታ አካላት ትጋት መሆኑን አንስተው ይህንኑ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ተናግረዋል። በመሆኑም የመንግስትን የልማት እቅዶችን በመደገፍና የሰላም ጥረቶችን በማገዝ የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የመንግስት የሰላምና የልማት ጥረት የሚደገፍ በመሆኑ ለሰላማዊ ሰልፍ መውጣታቸውን ተናግረው ለእኩይ ዓላማ የሚንቀሳቀሱ አካላት ከድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባም አንስተዋል። በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በህዝብ ስም እየማሉ ግድያ፣ ዘረፋ፣ እገታና ውንብድና የሚፈጽሙ ጽንፈኞችን በፅኑ እናወግዛለን፤ ለሰላማችንም ዘብ እንቆማለን ሲሉ ተናግረዋል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ፤ በሁሉም አካባቢዎች ህብረተሰቡ አንድነቱን በማጠናከር እያሳየ ያለውን ሁለንተናዊ ድጋፍና ተሳትፎ አድንቀዋል። ከውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በማበር ሀገርን ለማፍረስ የሚሰሩ ቡድኖች ከክህደት እና ሸፍጥ በመውጣት ለሀገር ልማትና እድገት በጋራ እንዲቆሙም ጠይቀዋል። የተጀመሩ ሀገራዊ የልማት እቅዶችን ከዳር በማድረስ ሀገራዊ ህብረ ብሄራዊ አንድነትና ሰላምን በማፅናት ሀገር መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል። በዛሬው እለት ከደሴ ከተማ በተጨማሪ በኮምቦልቻ፣ ሐይቅ እና ሌሎችም ከተሞች ተመሳሳይ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፎች ተካሂደዋል።
ሰላማችንን በማጽናት በከተማችን የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እንዲበቁ የድርሻችንን ለማበርከት ዝግጁ ነን
Jun 29, 2025 109
ጎንደር ፤ሰኔ 22/2017 (ኢዜአ) ሰላማችንን በማጽናት በከተማችን የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የድርሻችንን ለማበርከት ዝግጁ ነን ሲሉ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ሰላምን የሚደግፍና ጽንፈኝነትን የሚያወግዝ ህዝባዊ ሰልፍ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል፡፡ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ነዋሪዎች እንደተናገሩት ጎንደር በከፍተኛ የልማት ሥራ ላይ ትገኛለች፤ ሰላሙንና ልማቱን ለማስቀጠል ደግሞ እኛ ነዋሪዎች ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኞች ነን ሲሉ ተናግረዋል "ጎንደር የቀደመ ገናና ስሟንና ታሪኳን የሚመጥን የመልማት እድል ያገኘችው አሁን ነው" ያሉት በህዝባዊ ሰልፉ ላይ የተሳተፉት አቶ ጌትነት መንግስቱ ናቸው፡፡ ከተማዋ ያገኘችው ዘርፈ ብዙ የልማት እድሎች ለህዝቡ የዘመናት የልማት ጥያቄ መሰረታዊ ምላሽ የሚሰጡ በመሆናቸው ለሰላም ዘብ በመቆም ልማቱን ለማስቀጠል የድርሻቸውን ለማበርከት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ሌላዋ የሰልፉ ተሳታፊ ወይዘሮ አለምነሽ ብርሃኑ በበኩላቸው በከተማው እየተካሄዱ የሚገኙ የኮሪደር ልማትና የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ሥራዎች ታሪካችንን ያደሱ አኩሪ የልማት ተግባራት ናቸው ብለዋል፡፡ "ጎንደር በአሁኑ ወቅት ያገኘችው የልማት ዕድል በምንም መንገድ ወደኋላ ሊመለስና ሊቀለበስ የማይችል ነው" ያሉት ወይዘሮ አለምነሽ ለልማትና ለሰላም ጸር የሆነውን ጽንፈኝነት ለመታገል ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። በፌደራልና በክልሉ መንግስት ድጋፍ በከተማችን እየተካሄዱ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች በርካታ ወጣቶችን የሥራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ አስችሏል ያለው ደግሞ ወጣት መሃመድ አብዲ ነው፡፡ በለውጥና በአዲስ የእድገት ጎዳና ላይ የምትገኘው ሀገራችን ወጣቶች በሃገራቸው ብሩህ ተስፋ እንዲሰንቁና ለልማትና ሰላም ማስፈን እንዲተጉ መነሳሳት ፈጥሯል ብሏል። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በጎንደር ከተማ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን አስታውሰዋል። የከተማው ህዝብ ከዳር አስከ ዳር በመነሳት የልማት ሥራዎችን በገንዘብ፣ በጉልበቱና በእውቀቱ እየደገፈ መሆኑን የጠቆሙት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው፣ "ጎንደር ለሰላም ዋጋ የምትሰጥ ከተማ ነች" ብለዋል፡፡ ለከተማዋ እድገት አስተዋጽኦ ላደረጉ የፌደራልና የክልሉ አመራሮች እንዲሁም በሀገር ውስጥና በውጭ ላሉ ወገኖችም ምስጋና አቅርበዋል። በህዝባዊ ሰልፉ ላይ የመንግስት ሠራተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ማህበራዊ
በፍትሐ ብሄር ክርክር ወቅት የተቋማት አመራሮች አስፈላጊ መረጃዎችን አደራጅቶ የማቅረብ ልምድና በቂ ግንዛቤ ሊያዳብሩ ይገባል
Jun 30, 2025 47
ባህርዳር ፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ) ፡-በፍትሐ ብሄር ክርክር ወቅት የተቋማት አመራሮች አስፈላጊ መረጃዎችን አደራጅቶ የማቅረብ ልምድና በቂ ግንዛቤ ሊያዳብሩ እንደሚገባ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ። መንግስት ተከራካሪ በሆነባቸው የፍትሃ ብሄር ጉዳዮች በሚያጋጥሙ ችግሮችና መፍትሄዎች፤ የክልሉ ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅና የአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ በባህር ዳር እየተካሄደ ይገኛል። የመድረኩ ዓላማ የመንግስት ተቋማት የፍትሃ ብሄር ክርክር ሲያጋጥማቸው በጉዳዩ ላይ የተሟላ ዝግጅት በማድረግና አስፈላጊ መረጃዎችን ለፍርድ ቤቶች በማቅረብ የህዝብና የመንግስት ንብረቶችን ለመጠበቅ መሆኑም ታውቋል። በዚሁ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አለምአንተ አግደው፤ የመንግሥት ተቋማት የፍትሃ ብሄር ክርክር ሲያጋጥማቸው የሚስተዋሉ ክፍተቶች እየተበራከቱ መሆኑን አንስተዋል። የፍርድ ቤቶች ሚና ነፃ የዳኝነት አገልግሎት መስጠት መሆኑን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ፤ በክርክር ሂደት ከሚዛናቸው በመጉደል በተቋማት አሰራሮች የሚታዩ ክፍተቶችን ሊሸፍኑ የማይችሉ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህ ረገድ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ተቋማት አመራሮች ኃላፊነት ያለባቸው መሆኑን ገልጸው ይህ ሲባል ግን ፍርድ ቤቶች የመንግሥትና የሕዝብ ጥቅም በሚጎዳበት አጋጣሚ በዝምታ ይመለከታሉ ማለት አይደለም ብለዋል። በመሆኑም የመንግሥት ተቋማት የተቋሞቻቸውን ጉዳዮች በአግባቡ መምራትና የፍትሐ ብሔር ክርክር ሲያጋጥም አስፈላጊ ማስረጃዎችን በማቅረብ የህዝብን ሃብትና ንብረት መጠበቅና ማስከበር እንዳለባቸው አንስተዋል። የክልሉ መሬት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሰይፉ የሱፍ፤ በመንግስት የተያዙ የፍትሃ ብሄር ክሶች በአግባቡ ክርክር ስለማይደረግባቸው ከፍተኛ ሃብት እየታጣ መሆኑን ገልጸዋል። በፍርድ ቤቶች ከሚካሄዱ ክርክሮች በአብዛኛው መሬትና መሬት ነክ ጉዳዮች መሆናቸውን አንስተው ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ህግ አውጭውና ህግ ተርጓሚው ከአስፈፃሚው ጋር ተቀራርቦ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በምክክር መድረኩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የሚመለከታቸው አካላት እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎች እየተሳተፉ ነው።
መንግስት ያደረጋቸው የውጪ አገር የስራ ስምሪት ስምምነቶች ውጤት እያስመዘገቡ ነው
Jun 30, 2025 42
አዲስ አበባ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦መንግስት ያደረጋቸው የውጪ አገር የስራ ስምሪት ስምምነቶች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለበል ደሴ ገለጹ። መንግስት የውጪ አገር የስራ ስምምነቶችን በማድረግ የስራ ዕድል የሚፈልጉ ሰራተኞች ወደ መካከለኛው ምስራቅ በመጓዝ በተለያዩ የስራ ዘርፍ ተሰማርተው ይገኛሉ፡፡ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት " የዓለም አቀፍ ስደት መንስኤዎች፣ ፈተናዎች እና እድሎች" በሚል ርዕስ ያካሔደውን ጥናት ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ይፋ አድርጓል። የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለበል ደሴ በዚሁ ወቅት፤ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ እና ከአንዱ አገር ወደ ሌላው አገር የመሰደድ የሰው ልጆች ተፈጥሯዊ ባህሪ ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ህገ ወጥ ስደትን ለመከላከል እያከናወናቸው ያሉ የውጭ አገር የስራ ስምሪት ስምምነት እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን አንስተዋል፡፡ በዚህም ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረው፤ ነገር ግን አሁንም የሚቀሩ ስራዎች መኖራቸውን አመልክተዋል። ቀሪ ስራዎችን ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ስራ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ተመራማሪና የጥናቱ ተሳታፊ ሐና ወልደኪዳን በበኩላቸው እንደገለጹት፥ አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች ለህገ ወጥ ስደት የሚዳረጉት በተሳሳተ መረጃ ምክንያት ነው። ሌላ ሀገር በመሰደድ የስራ ዕድል ብቻና ጥሩ አጋጣሚ ለሚጠብቁ መጥፎ ክስተት ሊኖር እንደሚችልም ማሳወቅ እንደሚገባ ተናግረዋል። እንዲሁም ሰዎች ከአገር ለመውጣት ህገ ወጥ መንገድ ምርጫቸው እንዳይሆን፤ለህጋዊ የውጭ አገር የስራ ስምሪት አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን በአቅራቢያቸው ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል
Jun 30, 2025 51
ደብረ ብርሃን፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፡-በሰሜን ሸዋ ዞን በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ሲል የዞኑ አስተዳደር አሰታወቀ። "በጎነትና አንድነት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ሃሳብ የመጪው ክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ በደብረ ብርሃን ተካሄዷል። የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። በመጪው ክረምት በሚካሄደው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ሰላምን በዘላቂነት ለማረጋገጥና የነዋሪዎችን አብሮነት በማጠናከር ላይ ማተኮር እንዳለበት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በማህበረሰቡ ውስጥ ለዘመናት ባህል ሆኖ የቆየውን በጎ ተግባር በተደራጀ አግባብ በመምራት አረጋውያንን፣ ህጻናትንና ሌሎች ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል ብለዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ምትኩ ማሙሻ በበኩላቸው በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 780 ሺህ 172 ወጣቶች፣ ሴቶችና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎችን ለማሳተፍ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና፣ በመንገድ ጥገናና የአረጋዊያንን መኖሪያ ቤት በማደስና በሌሎች ልማቶች በመሳተፍ ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው ብለዋል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራውም መንግስት ያወጣው የነበረውን ከ687 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ለማዳን የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ በማካሄድ ላይ መሆኑንም አስረድተዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ወጣት ፌዴሬሽን ሰብሳቢ ወጣት ዮናስ ፀጋው በበኩሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የመተባበር፣ የመደጋገፍ፣ አብሮ የመስራትና በጋራ የመለወጥ ባህልን ለመማር የሚያስችል ነው ብሏል። በመጪው ክረምት በሚካሄደው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መላ አባላትን በንቃት በማሳተፍ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን ለማከናወን ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድቷል። ከሚዳ ወረሞ ወረዳ የመጣቸው የውይይቱ ተሳታፊ ወጣት ኤደን ተገኝ በበኩሏ አባላት የተገኘውን ሰላም ዘላቂ በማድረግ፣ በሰላምና እሴት ግንባታ ላይ በማተኮር የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱን እንደሚያከናውኑ ገልጻለች። በበጀት ዓመቱ የበጋ ወራት በተካሄደው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 405 ሺህ 429 የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ 309 ሚሊዮን 791 ሺህ ብር ግምት ያለው ተግባር መፈጸም መቻሉም ተመላክቷል።
ተማሪዎች በተዘጋጁት ልክ ፈተናውን በተረጋጋ መንፈስ መውሰድ አለባቸው
Jun 30, 2025 54
ሆሳዕና፣ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፦ ተማሪዎች በተዘጋጁት ልክ ፈተናውን በተረጋጋ መንፈስ መውሰድ እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ። እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና እየወሰዱ ያሉ ተማሪዎችን አበረታተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በሀገር አቀፍ ፈተና የተቀመጡ ተማሪዎችን ውጤታማ ለማድረግ የማጠናከሪያ ትምህርት ከመስጠት ባለፈ በሞዴል ፈተናዎች የማለማመድ ሥራ ሲሰራ ቆይቷል። ተፈታኝ ተማሪዎች በራሳቸው እንዲተማመኑም በስነልቦና የማዘጋጀት ሥራ በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመዋል። ተማሪዎች በተዘጋጁት ልክ ፈተናውን በተረጋጋ መንፈስ መውሰድ እንዳለባቸውም ጠቁመዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በበኩላቸው እንዳሉት፣ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ሥራ ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ግብአት ከማሟላት በተጨማሪ መምህራን ተማሪዎችን የማብቃት ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡም የድጋፍና ክትትል ሥራ መከናወኑንም አስታውሰዋል። እንደ አቶ አንተነህ ገለጻ፥ በክልሉ ከ35 ሺህ በላይ ተማሪዎች ዛሬ የተጀመረውን ሀገር አቀፍ ፈተና እየወሰዱ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ ፈተናውን በበይነ መረብ እየወሰዱ ያሉት 6 ሺህ 884 ተማሪዎች ናቸው፡፡
ኢኮኖሚ
ኢትዮጵያ የባለብዙ ወገን ግንኙነቷን ለማጠናከር እና የስትራቴጂክ አጋርነቷን ለማስፋት ቁርጠኛ መሆኗን ገለጸች
Jun 30, 2025 45
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የባለብዙ ወገን ግንኙነቷን ለማጠናከር እና የስትራቴጂክ አጋርነቷን አድማስ የበለጠ ማስፋት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አስታወቀች። 10ኛው የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ (AIIB) ዓመታዊ ስብስባ በቻይና ቤጂንግ ተካሄዷል። በስብስባው ላይ የገንዘብ ሚኒስትር እና የ2024/25 የባንኩ አስተዳደሪዎች ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አሕመድ ሽዴ ተሳትፈዋል። ሚኒስትሩ ከስብስባው ጎን ለጎን ከፋይናንስ ተቋማት እና የልማር አጋሮች ጋር የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን አድርገዋል። ከተሰናባቹ የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ ጂን ሊኪን ጋር በነበራቸው ቆይታ ጂን የ10 ዓመት የአገልግሎት ቆይታቸው ባንኩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ክብር የሚሰጠው ተቋም እንዲሆን ያከናወኑትን ስራ አድንቀዋል። በውይይቱ ባንኩ ትራንስፖርት፣ ኢነርጂ እና የማዘጋጃ ቤታዊ መሰረተ ልማት ጨምሮ በኢትዮጵያ ያለውን ተሳትፎ ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል። የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከቻይና የፋይናንስ ሚኒስትር እና የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ የገዢዎች ቦርድ ሰብሳቢ ላን ፎአን፣ ከኳታር የፋይናንስ ሚኒስትር አሊ አል ኩዋሪ ጋር ተወያይተዋል። ሚኒስትሩ ከቻይና ልማት ባንክ፣ ለቻይና የኤክስፖርት እና ኢምፖርት ባንክ እና ከይና ኢንዱስትሪና ንግድ ባንክ አመራሮች ጋርም ተነጋግረዋል። ውይይቶቹ በልማት ፋይናንስ፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ማፋጠን እና የኢትዮጵያን የእድገትና የማይበገር አቅም መገንባት አጀንዳ የኢኖሼሽን አማራጮችን ተጠቅሞ መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የባለብዙ ወገን ግንኙነቷን ለማጠናከር፣ የአረንጓዴና ሁሉን አቀፍ እድገትን ለማሳለጥ እንዲሁም ለኢትዮጵያውያን እና አፍሪካ ውጤቶችን የሚያስገገኙ ስትራቴጂካዊ አጋርነቶችን ለማስፋት ቁርጠኛ መሆኗን ገልጻለች። በተጨማሪም ኢትዮጵያ የ10 ዓመት የልማት እቅዷ እና ለሰፊው ቀጣናዊ ትስስር አጀንዳዋ ድጋፍ እንዲያገኝ ከእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ እና ሌሎች ተቋማት ጋር በትብብር እንደምትሰራ የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል ያላትን የጸና ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው- ሚኒስትር አህመድ ሽዴ
Jun 30, 2025 49
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል እና ከባቢ አየርን ለመጠበቅ ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ። 10ኛው የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ (AIIB) ዓመታዊ ስብሰባ በቻይና ቤጂንግ ተካሄዷል። በስብሰባው ላይ የገንዘብ ሚኒስትር እና የ2024/25 የባንኩ አስተዳደሪዎች ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አሕመድ ሽዴ ተሳትፈዋል። የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ፣ የባንኩ ዓለም አቀፍ አባል ሀገራት እና ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በስብሰባው ላይ ተሳትፎ አድርገዋል። የገንዘብ ሚኒስትር እና የ2024/25 የባንኩ ገዢዎች ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አሕመድ ሽዴ በስብሰባው ላይ የኢትዮጵያ ሪፎርም እና የልማት ግቦችን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የላቀ አመራር ሰጪነት ለውጥ እያስመዘገበች እንደምትገኝ ገልጸዋል። ለውጡ የተገኘው በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ እንደሆነና የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለመፍጠር፣ የግሉን ዘርፍ ኢንቨስትመንት ለማሳደግ፣ የአስተዳደር አቅምን ለማሻሻል እንዲሁም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የማይበገር እና ከወቅቱ ጋር የሚራመድ ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንዳለው አመልክተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና ከባቢ አየርን ለመጠበቅ ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያመላክት ነው ብለዋል። የኢኮኖሚ ሪፎርሙ እና የአረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ፈተናዎች ሁሉን አቀፍ፣ ጊዜው የደረሰባቸው የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል አማራጮች እና ሀገር በቀል መፍትሄዎችን ለማበጀት ያላትን የአመራር ቁርጠኝነት አንስተዋል። የገንዘብ ሚኒስትር እና የ2024/25 የባንኩ አስተዳዳሪዎች ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ አሕመድ ሽዴ የእስያ የመሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ባንክ ገዢዎች የንግድ የጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር በአወያይነት መርተዋል። ውይይቱ በዘላቂ ትስስር እና መሰረተ ልማት ላይ ያተኮረ ነው። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #Ethiopia #ኢትዮጵያ
የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ የዶሮ እርባታ ፕሮጀክት የ50 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ያደርጋል-የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አዴሲና
Jun 30, 2025 50
አዲስ አበባ ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ልማት ባንክ የሌማት ትሩፋት አካል ለሆነው የኢትዮጵያ የዶሮ እርባታ ፕሮጀክት የ50 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑን የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አዴሲና ገለጹ። ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ ዛሬ በስፔን ሲቪያ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) የተመራ ልዑካን ቡድን ኢትዮጵያን ወክሎ በኮንፍረንሱ ላይ እየተሳተፈ ነው። “Global Alliance Against Poverty and Hunger” ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን ያዘጋጀው ስብሰባ ተካሄዷል። የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሌማት ትሩፋት ዙሪያ ያላት ልምድ እንደ ተምሳሌታዊ ፕሮጀክት በስብሰባው ላይ አቅርበዋል። በተጨማሪ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የምታደርጋቸውን ሌሎች ሰፋፊ ጥረቶች አስመልክቶ ያላትን ተሞክሮም አጋርተዋል። ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል። ኢኒሼቲቩ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ሀገር በቀል ሀሳቦችን እና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ መሆኑን አመልክተዋል። በመንግስት እና በህዝቡ በባለቤትነት የተያዘ መሆኑ፣ድህነትን በመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አንጻር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ተናግረዋል። በተጨማሪም ኢኒሼቲቭ በሀገር ውስጥ ሀብት ላይ በመመስረት የሚተገበር መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ለምታደርጋቸው ትብብሮች ለኢኒሼቲቩ ድጋፍ በማፈላለግ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና ሊኖረው ይችላል ነው ያሉት ሚኒስትሩ። አክለውም ኢኒሼቲቩን በተጨማሪ ኢንቨስትመንት በስፋት መተግበር እንደሚቻል ገልጸው፥ ለዚህም የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ የተገበረው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎረም ለውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አመልክተዋል። በመጨረሻም ኢትዮጵያ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከሌሎች ሀገራት መልካም ተሞክሮ ለመማርም ዝግጁ ናት ብለዋል። የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አዴሲና በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት በሰራችው አመርቂ ስራ በስንዴ ምርት ሙሉ በሙሉ ራሷን መቻሏን ገልጸዋል። በትኩረት ተገቢው አመራር እና ድጋፍ ከተደረገ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንደሚቻል የኢትዮጵያ ስኬት እንደ ተጨባጭ ማሳያ ሊወሰድ እንደሚችል አመልክተዋል። ፕሬዝዳንቱ ባንኩ የኢትዮጵያ የሌማት ትሩፋት አካል የሆነውን የዶሮ እርባታ ፕሮጀክት 50 የሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለመደገፍ መወሰኑን ይፋ አድርገዋል። ኮንፍረንሱ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል። የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን በሚኖሩ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ ተሳትፎ ያደርጋል።
ግብርናውን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ አማራጭ የኤክስቴንሽን አገልግሎቶችን ማስፋት ይገባል - ቋሚ ኮሚቴው
Jun 30, 2025 46
አዲስ አበባ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦በምግብ ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካትና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አማራጭ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎቶችን ማስፋት እንደሚገባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ። ቋሚ ኮሚቴው የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ የአስረጂ መድረክ አካሂዷል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ለግብርና ዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው። የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ተደራሽነት ለማስፋት፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በመድረኩ ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላትና ከሕግ ባለሙያዎች ለተነሱ ጥያቄዎች የግብርና ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅት የግብርና ዘርፉ የአገሪቷ ኢኮኖሚ መሰረት እንደመሆኑ ተደራሽና ጥራቱን የጠበቀ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ለማስፋት ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱ ተገልጿል። የምክር ቤቱና የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የምክር ቤቱ የሕግ ክፍል ባለሙያዎችም ረቂቅ አዋጁ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ ጠይቀዋል። ከተነሱ ጥያቄዎች ውስጥ መንግስት ቀደም ሲል በብቸኝነት በነፃ ይሰጥ የነበረውን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ለምን በክፍያ መስጠት አስፈለገ የሚለው አንዱ ነው። በሌላ በኩል የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ላይ የሚሳተፉ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የክፍያ ሥርዓትን በተመለከተ ጥያቄ ተነስቷል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) መንግስት መደበኛ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን በተደራጀና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ መስጠቱን ይቀጥላል ነው ያሉት። ይሁንና እያደገ ያለውን የግብርና ኤክስቴንሽን ፍላጎት ለማሟላት አማራጭ አገልግሎት ሰጪዎችን ማካተት ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑንም ነው ያነሱት። የግብርና ሚኒስቴር አማካሪ ተፈራ ዘርዓይ በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፣ የግብርና ኤክስቴንሽን ሥራ በመንግስት ብቻ ሲከወን መቆየቱን ገልጸዋል። የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ፣ በመንግስት ብቻ ይሰጥ የነበረውን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት በተለያዩ ወገኖች እንዲሰጥ በማድረግ ተደራሽነትን ማስፋት ያስችላል ነው ያሉት። ይህም አሁን ላይ በግብርናው ዘርፍ እየታየ ያለውን እመርታ የበለጠ ለማሳደግና በዘርፉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስተዋወቅና ለመጠቀም እንደሚያስችልም አብራተዋል። ረቂቅ አዋጁ የግብርና ቢዝነስ ምንነት ላይ በቂ ማብራሪያ እንዲሰጥ ተጠይቋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ፤ ግብርና አንድ አዋጭ የቢዝነስ ዘርፍ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል ብለዋል። ረቂቅ አዋጁ በዚህ ረገድ የግብርና ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅና ጥቅም ላይ ማዋል እንዲሁም የግብርና ቢዝነስን ለማስፋት ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ፤ ረቂቅ አዋጁ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ተደራሽነት ለማስፋት ያስችላል ብለዋል። ኢትዮጵያ አሁን ላይ ለግብርና ዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኑንና በዚህም በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውን ያነሱት ሰብሳቢው፤ በተለይም በምግብ ራስን ለመቻልና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተያዘው ግብ እውን እንዲሆን የረቂቅ አዋጁ መዘጋጀት ወሳኝ ነው ብለዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓም ባደረገው 32ኛ መደበኛ ስብሰባ የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መምራቱ ይታወሳል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢትዮጵያ የጨረር ህክምና ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jun 30, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የካንሰር ምርመራን ጨምሮ የጨረር ህክምና ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የጤና ሚኒስቴር ከዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር "የተስፋ ጨረሮች በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጁትና አቶሚክ ኢነርጂ በጤናው ዘርፍ ባለው ጠቀሜታ ዙሪያ የሚመክር ዓለም አቀፍ ጉባኤ በአፍሪካ ህብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል። በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ጀነራል ራፋኤል ግሮሲ፣ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ታድመዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት፥ የዓለም የጤና አውድ እየተቀየረ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያም ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን ታሳቢ ያደረገ የጤና ስርዓት እየገነባች ነው ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በጤና ኤክስቴንሽን አማካይነት በተሰራው ስራ የበርካቶችን ጤና አጠባበቅ ማሻሻል መቻሉን ገልጸዋል። በርካታ የጤና ባለሙያዎችም ሰልጥነው አገልግሎት እየሰጡ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በሁሉም አካባቢ የጤና አገልግሎትን በጥራት ተደራሽ የማድረግ ጉዞ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። ኢትዮጵያ የካንሰር ምርምራና የጨረር ህክምና ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝ በማንሳት፥ ለዚህም ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም መጀመሯን ጠቁመዋል። የጨረር ህክምና በጥንቃቄ እና በኃላፊነት ጥቅም ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋቱን አመላክተዋል። የኑክሌር ኢነርጂን ለጤና አገልግሎት በማዋል የጨረር ህክምናን ማስፋት የካንሰር በሽታን በፍጥነት በምርመራ በመለየት የሰዎችን ህይወት ለመታደግ ትልቅ ሚና እንዳለውም ነው የገለጹት። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘውም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የህብረተሰብን ጤና በማሻሻል ንቁና ጤናማ አኗኗርን እያጎለበተ መሆኑን አንስተዋል። የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የኑክለር ኢነርጂን ለሰላማዊ አገልግሎት በተለይም ለጤናው ዘርፍ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያደርጋቸው ድጋፎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የልማት አጋሮች እና መንግስታት ከፈንድ ባሻገር የዓለም ጤና ውጤት ፈጣሪዎች በመሆን የትብብር አድማሳቸውን ከፍ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።
ሥራ ፈጣሪዎች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር መቀየር የሚችሉበት ምቹ ስነ ምህዳር መፍጠር ተችሏል
Jun 29, 2025 101
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦ሥራ ፈጣሪዎች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር መቀየር የሚችሉበት ምቹ ስነ ምህዳር መፍጠር መቻሉን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለፁ። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) የፈጠራ ሀሳብ በማቅረብ ስታርት አፕ ለመጀመር እየተደረገ ያለውን ዝግጅት በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት፤ የፈጠራ ሥራዎች ለአንድ ሀገር እድገት መሰረት በመሆናቸው ዘመኑን የዋጁ የፈጠራና የምርምር ሥራዎች ማስፋት ያስፈልጋል። ወጣቶች በፈጠራና ምርምር ሥራዎች እንዲሳተፉ ትኩረት መደረጉን አንስተው፤ ለውጤታማነቱም አስቻይና የጎለበተ ምህዳር መፍጠር እንደሚገባ አንስተዋል። ስታርት አፕ በዋነኝነት የወጣቶችን ሃሳብ መሰረት ያደረገ የፈጠራ ስራ ውጤቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ሃሳብን ወደ ተግባር መለወጥ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የአንድ ሀገር እድገት እና ብልፅግና መሠረት የሚያደርገው ጥራት ባለው በፈጠራ ሥራ ውጤቶች በመሆኑ በትኩረት መሥራት እንደሚገባም ተናግረዋል። በዚህም የፈጠራ ስራ ውጤት ለሆነው ስታርት አፕ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ሕጋዊ አሰራሮችን በመዘርጋት ምቹ ምህዳር ለመፍጠር ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። አሁን ላይ በኢትዮጵያ የፈጠራ ሥራ ሃሳባቸውን መቀየር የሚያስችል ምቹ ምህዳር መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል። የግል ዘርፉ በስታርታ አፕ እና ሌሎች የፈጠራ ሥራዎች እንዲሳተፍ የዘርፉ ምህዳር እንዲሰፋ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ተቋማት ለችግር ፈቺ የምርምርና ኢኖቬሽን ሥራዎች መጠናከር አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል። ስታርት አፕ ለኢትዮጵያ አዲስ እንደመሆኑ በርካታ ወጣቶች ወደ ዘርፉ የመግባት ፍላጎቶች እየጨመረ መሆኑን አንስተው፤ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር አንዱ የህግ ማእቀፍ በመሆኑ በሂደት ላይ ነው ብለዋል። የህግ ማዕቀፉ ፀድቆ ወደ ተግባር ሲገባ አጠቃላይ የስታርት አፕ ስነ ምህዳሩን የሚያጎለብትና የፈጠራ ሃሳብ ላላቸው ወጣቶች ተስፋን የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል። በዘርፉ ተሳታፊ ወጣቶች በበኩላቸው በኢትዮጵያ ለስታርት አፕ ልዩ ትኩረት መሰጠቱና ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም አድንቀዋል። ወጣት ናትናኤል አዳነ በበኩሉ አገልግሎት የሰጡ የፕላስቲክ ቁሳቁሶችን መልሶ በመጠቀም የኮንስትራክሽን ግብዓት የሆኑ ምርቶች ማምረት ላይ መሰማራቱን ተናግሯል። መንግስት ባደረገለት የገንዘብ እና ሌሎች ድጋፎች ፈጥኖ ወደ ስራ ለመግባት እንዳስቻለው ተናግሯል። ወጣት ሳሙኤል ዘነበ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የጤና አገልግሎት ላይ ተሰማርቶ በአዲስ አበባ ውጤታማ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፆ፤ በቀጣይ ስራውን ወደ ተለያዩ ክልሎች አስፍቶ ለመስራት ማቀዱን ተናግሯል።
የምስራቅ አፍሪካ የስልጠና ልህቀት ማዕከል ለመሆን የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው
Jun 29, 2025 114
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በምስራቅ አፍሪካ የስልጠና ልህቀት ማዕከል ለመሆን የሚያስችል የአቅም ግንባታ እና ሎጂስቲክስ የማሟላት ስራ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የኢትዮጵያ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ታመነ ሀይሉ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአቅም ግንባታ ስራ ኢንስቲትዩቱ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንደኛው ነው። ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ ያለውን ችግር በመለየት ስልጠና እየሰጠ መሆኑንና እስካሁን ባለው ከ18 አገራት ለተውጣጡ ከ200 በላይ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠቱን ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ የምስራቅ አፍሪካ የስልጠና ልህቀት ማዕከል የመሆን ርዕይውን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ ያሉ ችግሮችን በጥናት በመለየት መፍትሄ ከማበጀት ባለፈ ዘመናዊ ላቦራቶሪ እየገነባ መሆኑንም ነው የገለጹት። በውሃ ዘርፍ ላይ ስልጠና ለሚሰጡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው በአመት የሚያሰለጥናቸው ባለሙያዎች ቁጥር እያደገ መምጣቱንም አብራርተዋል። ኢንስቲትዩቱ ከ10 አመት በፊት በአመት 150 የሚጠጉ ባለሙያዎችን ያሰለጥን እንደነበር አንስተው አሁን ላይ ከ2ሺህ በላይ ሰልጣኞችን በአመት እየተቀበለ መሆኑን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አገልግሎቱን በማስፋት ዘርፉ የሚፈልገውን ድጋፍ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የኢንስቲትዩቱ ላቦራቶሪ አለም አቀፍ እውቅና ለማግኘት ሰነድ መዘጋጀቱን ገልፀው፤ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የሚያስችለውን ስራ እያከናወነ ነውም ብለዋል።
የኢትዮጵያን የልማት ጉዞ ለማሳካት ችግር ፈቺ ምርምሮችን ወደ ተግባር የመለወጥ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት
Jun 28, 2025 118
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የልማት ጉዞ ለማሳካት ችግር ፈቺ ምርምሮችን ወደ ተግባር የመለወጥ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት፣ ስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አመራሮች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ተመራማሪዎች፣ የፈጠራ ባለሙያዎችና የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች የተሳተፉበት የምርምርና ኢኖቬሽን አውደ ጥናት መካሄድ ጀምሯል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያ ትልቅ ህልም ሰንቃ የዜጎችን ህይወት ሊቀይሩ የሚችሉ የልማት ስራዎች ተግባራዊ እያደረገች ትገኛለች። ሁለንተናዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጡ የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ወጣቶች እንዲበራከቱ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን የማሻሻል ስራ መሰራቱንም አስታውቀዋል። በተከናወኑ ተግባራት ሁለንተናዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጡ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለያዘችው የልማት ጉዞ የምሁራን የጥናትና ምርምር ስራዎች መሬት ላይ ወርደው የዜጎችን ህይወት መቀየር እንዲችሉ የሚሰራው ስራ መጠናከር እንዳለበት አመልክተዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ መንግስት ባለፉት ዓመታት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፉን በማጎልበት ወጣቶችን በፈጠራ ስራዎች በሰፊው ለማሳተፍ መስራቱን ገልጸዋል፡፡ በሳይንስና ቴክኖሎጂ በመታገዝ የሚደረጉ የጥናትና ምርምር ስራዎች ሊበራከቱ እንደሚገባም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።
ስፖርት
በፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫ ሁለት የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ
Jun 30, 2025 64
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፦ በፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ የሶስተኛ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ምሽት 4 ሰዓት ላይ ኢንተር ሚላን ከፍሉሜኔንሴ በባንክ ኦፍ አሜሪካ ስታዲየም ይጫወታሉ። የዘንድሮው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ተፈላሚ የነበረው ኢንተር ሚላን በምድብ አምስት በሰባት ነጥብ የምድቡ መሪ በመሆን ማጠናቀቀቁ የሚታወስ ነው። ፍሉሜኔንሴ በምድብ ስድስት በአምስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ጥሎ ማለፉ ገብቷል። ሁለቱ ክለቦች ከዚህ ቀደም እርስ በእርስ ተገናኝተው አያውቁም። ጨዋታው በኢንተር ሚላን የማጥቃት አቅም እና የፍሉሜኔንሴ አይበገሬ የተከላካይ ክፍል መካከል የሚደረግ ጦርነት የሚል ስያሜ አግኝቷል። በዓለም ዋንጫው በሶስት ጨዋታዎች ሁለት ግቦችን ያስቆጠረው የ27 ዓመቱ የኢንተር ሚላን አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ እና የ40 የፍሉሜኔንሴ አንጋፋ ተከላካይ ቲያጎ ሲልቫ የሚኖራቸው ፍጥጫ ይጠበቃል። ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በካምፒንግ ወርልድ ስታዲየም ማንችስተር ሲቲ ከአል ሂላል ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በምድብ ሰባት የነበረው ማንችስተር ሲቲ በዘጠኝ ነጥብ ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱ ይታወቃል። ሰማያዊዎቹ በውድድሩ የምድቡን ሁሉንም ጨዋታ ያሸነፈ ብቸኛ ክለብ ነው። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ጁቬንቱስን 5 ለ 2 ሲያሸንፍ ያሳየው ድንቅ ብቃት የዋንጫ ተገማችነቱን የበለጠ አሳድጎታል። የሳዑዲ አረቢያው አል ሂላል በምድብ ስምንት ሪያል ማድሪድን ተከትሎ በአምስት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅሏል። ሁለቱ ክለቦች እ.አ.አ በ2012 በቅድመ ውድድር የወዳጅነት ጨዋታ ላይ ተገናኝተው አል-ሂላል 1 ለ 0 አሸንፏል። ማንችስተር ሲቲ ጨዋታውን የማሸነፍ ትልቅ ግምት ቢያገኝም ከተጋጣሚው ብርቱ ፉክክር ይጠብቀዋል። የጨዋታዎቹ አሸናፊዎች በሩብ ፍጻሜው የሚጫወቱ ይሆናል። በአሜሪካ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የፊፋ ክለቦች የዓለም ዋንጫ ዛሬ 17ኛ ቀኑን ይዟል።
ፒኤስጂ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል
Jun 30, 2025 89
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሃ ግብር የአውሮፓ ሻምፒዮኑ ፒኤስጂ ኢንተር ሚያሚን 4 ለ ዐ በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል። ማምሻውን በሜርሴዲስ-ቤንዝ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጇኦ ኔቬስ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ አሽራፍ ሃኪሚ እና የኢንተር ሚያሚው ቶማስ አቪሌስ በራሱ ግብ ላይ ቀሪዎቹን ጎሎች አስቆጥረዋል። ፒኤስጂ በጨዋታው በኢንተር ሚያሚ ላይ ፍጹም የጨዋታ የበላይነት የወሰደ ሲሆን የሚያሚ ተጫዋቾች ከራሳቸው የግብ ክልል ለመውጣትና ወደ ተጋጣሚ ቡድን መጫወቻ ስፍራ ለመድረስ እጅጉን ተቸግሮ ታይቷል። የፓሪሱ ክለብ ጠንካራ የመከላከል አቅም፣ አስደማሚ የመሐል ሜዳ ጨዋታ እና ማራኪ የማጥቃት እንቅስቃሴን ኢንተር ሚያሚ ሊቋቋም አልቻለም። በሊዮኔል ሜሲ እና ሉዊስ ሱዋሬዝ ልዩነት ፈጣሪነት ላይ ጥገኛ የሆነው ኢንተር ሚያሚ በጨዋታው የፒኤስጂ ፍጹም ቅጣት ክልል መድረስ ተራራን የመግፋት ያህል ከብዶት ነበር። የአውሮፓ ሻምፒዮኑ ፒኤስጂ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለ ሶስተኛ ቡድን ሆኗል።
ባየር ሙኒክ ወደ ሩብ ፍጻሜ አለፈ
Jun 30, 2025 68
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦ በፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ባየር ሙኒክ ፍላሚንጎን 4 ለ 2 አሸንፏል። ማምሻውን በሃርድ ሮክ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሃሪ ኬን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ሊኦን ጎሬትዝካ እና የፍላሚንጎው ኤሪክ ፑልጋር በራሱ ግብ ላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጌርሰን በጨዋታ እና ጆርጂኒዮ በፍጹም ቅጣት ምት ለፍላሚንጎ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ጨዋታው ተመጣጣኝ እና አዝናኝ ፉክክር ተደርጎበታል። ባየር ሙኒክ ሩብ ፍጻሜ ገብቷል። በሩብ ፍጻሜው ባየር ሙኒክ ከፒኤስጂ የፊታችን ቅዳሜ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ዛሬ በተደረገ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ፒኤስጂ ኢንተር ሚያሚን 4 ለ 0 አሸንፏል።
ኢንተር ሚያሚ ፒኤስጂን በማሸነፍ ዓለምን ያስደምም ይሆን?
Jun 29, 2025 81
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2017 (ኢዜአ)፦ በፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ፒኤስጂ እና ኢንተር ሚያሚ ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ጨዋታው ምሽት 1 ሰዓት ላይ በሜርሴዲስ ቤንዝ ስታዲየም ይደረጋል። የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው ፒኤስጂ በነበረበት ምድብ ሁለት በስድስት ነጥብ የምድቡ መሪ በመሆን አጠናቋል። ኢንተር ሚያሚ በምድብ ሁለት በአምስት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ወደ 16 ውስጥ ገብቷል። ሁለቱ ክለቦች እርስ በእርስ ሲገናኙ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። የኢንተር ሚያሚው አምበል እና አርጀንቲናዊው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ከቀድሞ ክለቡ ፒኤስጂ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ የዓለምን ትኩረት ስቧል። ሜሲ ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2023 በፓሪሱ ክለብ የቆየ ሲሆን በቡድኑ በነበረው ቆይታ ደስተኛ እንዳልሆነ ገልጾ ነበር። ጨዋታው አርጀንቲናዊው ምትሃተኛ ፒኤስጂ ለሱ የሰጠው ግምት ትክክል አለመሆኑን የሚያሳይበት መልካም አጋጣሚ ፈጥሮለታል። የኢንተር ሚያሚው አሰልጣኝ ሃቪየር ማሻራኖ ሜሲ ከቀድሞ ክለቡ ጋር በንዴት መጫወቱ እኛን ይጠቅመናል፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሲሆን ምርጥ ብቃቱን የበለጠ አውጥቶ ያሳያል ሲል ገልጿል። ሜሲ፣ ማሻራኖ፣ ራሞን ጆርዲ አልባ እና ሉዊስ ሱዋሬዝ በባርሴሎና አሰልጣኛቸው ከነበሩት የአሁኑ የፒኤስጂ አለቃ ሉዊስ ኤነሪኬ ጋር ይገኛሉ። የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው ፒኤስጂ ጨዋታውን የማሸነፍ ሰፊ ግምት አግኝቷል። ቡድኑ ባለው በጠንካራ ተከላካይ ክፍሉ እና በአስፈሪው የፊት መስመር ታግዞ ጨዋታውን እንደሚያሸንፍ የኳስ ልሂቃኑ በመናገር ላይ ይገኛሉ። ለጥቃት ተጋላጭ የተከላካይ ክፍል መስመር ያለው እና በውስን ተጫዋቾች ብቃት ላይ የተንጠለጠለው ኢንተር ሚያሚ ማንም ያልጠበቀውን ድል ሊያስመዘግብ ይችላል የሚሉ ተንታኞችም አልጠፉም። ሌላኛው የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ፍላሚንጎ እና ባየር ሙኒክን ምሽት 5 ሰዓት ላይ በሃርድ ሮክ ስታዲየም ያገናኛል። ፍላሚንጎ በምድብ አራት በሰባት ነጥብ አንደኛ፣ ባየር ሙኒክ በምድብ ሶስት በስስድስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዘው ማጠናቀቃቸው ይታወቃል። የታክቲክ ጦርነት ይደረግበታል በተባለበት በዚህ ጨዋታ ፍላሚንጎ ፈጣን የማጥቃት ሽግግሩ እና ኳስ ይዘው የሚጫወቱት አማካዮቹ በጨዋታው ላይ ልዩነት እንደሚፈጥሩ እየተነገረ ይገኛል። ባየር ሙኒክ ጥራት ያላቸውን ተጫዋቾች ሰብስቦ መያዙ እና የቡድን ጥልቀቱ በአንጻራዊነት የማሸነፍ እድል እንዲሰጠው አድርጎታል። የዛሬ ጨዋታ አሸናፊዎች በሩብ ፍጻሜው ይገናኛሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በሲዳማ ክልል የአረንጓዴ አሻራ ልማት ውጤቶችን በማስቀጠል የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋን ለመከላከል እየተሰራ ነው
Jun 30, 2025 46
ሀዋሳ፤ ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል በአረንጓዴ አሻራ ልማት የተገኙ ውጤቶችን በማስቀጠል የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋን በዘላቂነት ለመከላከል እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። ''በመትከል ማንሰራራት'' በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ልማት በዳራ ኦቲልቾ ወረዳ ሾይቾ ቀበሌ ዛሬ ተጀምሯል፡፡ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በእዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሥራዎች ዘርፈ ብዙ ውጤቶች ተመዝግዋል፡፡ በዚህም የተራቆቱ መሬቶች፣ የደረቁ ወንዞችና ጅረቶች መልሰው በማገገማቸው የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባሻገር ምርታማነት ለመጨመርና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያስቻሉ መሆኑን ገልጸዋል። በአረንጓዴ አሻራ ልማት የተገኙ ውጤቶችን ቀጣይነት በማረጋገጥ በክልሉ ሊገጥም የሚችለውን የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ ለመከላከል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ልማት የክልሉ ህዝብና መንግስት የህልውና ጉዳይ ነው ያሉት አቶ ደስታ፣ ልማቱ ባህል እየሆነ በመምጣቱ ለትውልድ እንዲሻገር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል። የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሥራ የህዝቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም አቶ ደስታ ገልጸዋል፡፡ ዛሬ ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ልማት የተጀመረበት ቀበሌ ከዚህ ቀደም የተራቆተ እንደነበር አስታውሰው፣ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአካባቢው ስነምህዳር መቀየሩንም ጠቅሰዋል፡፡ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ሃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ከ23 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት በአረንጓዴ ለማልማት ታቅዶ ወደስራ ተገብቷል፡፡ በክልሉ በመርሃ ግብሩ ከሚተከሉ ችግኞች 60 ከመቶ የሚሆኑት ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የሚሰጡና ቡና ቀዳሚው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የደን ሽፋንን የሚያሳድጉ፣ ለምግብነትና ለእንሳሰት መኖነት የሚውሉ እንዲሁም ለኢኮ ቱሪዝም የሚጠቅሙ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው፣ ለሚተከሉ ችግኞች ህዝቡን ባለቤት ለማድረግ ይሰራል ብለዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች የደን ሽፋንን በማሳደግ፣ የተጎዱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግና እና የመሬት ለምነትን በመጨመር ምርታማነትን አሳድገዋል ሲሉም ሃላፊው ተናግረዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ትውልድንና ሃገርና የሚያስቀጥል ሥራ በመሆኑ ሁሉም በሃላፊነት እየተሳተፈ መሆኑንና እሳቸውም የድርሻቸውን ለመወጣት በመርሃ ግብሩ መገኘታቸውን የተናገሩት ደግሞ በኩረ ትጉሃን ቀሲስ አማረ ግርማ ናቸው፡፡ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው፣ የተተከሉ ችግኞችን በአግባቡ መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የክልሉ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጡ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል
Jun 30, 2025 69
ክልል ፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ) ፦ በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጡ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። በክልሉ የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በነገው እለት እንደሚጀመርም ተመላክቷል። የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ተከላ አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ባለፉት ስድስት ዓመታት ከ6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ላይ የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን ጠቅሰው፣ ከተተከሉ ችግኞች መካከል 88 በመቶ የሚሆኑት መጽደቃቸውን ተናግረዋል። የአረንጓዴ ልማት ሥራው የውሃ አማራጮት እንዲሰፉ፣ በተፈጥሮ ሀብት መራቆት የደረቁ ሐይቆችና ወንዞች መልሰው እንዲያገግሙ ማድረጉንም ተናግረዋል። ከዚህ ባለፈ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትና እንዲረጋገጥ ማድረጉን ገልጸዋል። ልማቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል በዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በበጋ ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በተከናወነባቸው የተራቆቱ መሬቶች ችግኝ የመትከል ስራ እንደሚከናወን ጠቅሰዋል። ለዚህም በክልሉ በ38 ሺህ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ላይ ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጡ ችግኖች መዘጋጀታቸውን አስታውሰዋል። ችግኞቹን ለመትከል 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን ገልጸው፣ ለተከላ ከተዘጋጁት ችግኝ መካከል 40 በመቶው ለደን አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በተጨማሪም 30 በመቶ የሚሆኑት ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ፣ 19 በመቶ ለእንስሳት መኖ እና 10 በመቶው ለምግብ የሚውሉ ሲሆን ቀሪው ለውበት እንደሚውሉ አቶ ጌቱ አስታውቀዋል። የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩን ስኬታማ ለማድረግ ህዝቡ እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ በስፋት እንዲሳተፍም ጥሪ አቀርበዋል።
አረንጓዴ አሻራ የግብርና ምርታማነትን ከማሳደግ ጀምሮ በሁሉም የልማት መስኮች ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል
Jun 30, 2025 78
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ አረንጓዴ አሻራ የግብርና ምርታማነትን ከማሳደግ ጀምሮ በሁሉም የልማት መስኮች ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን ሚኒስትሮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማ፣ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር መካሄዱ ይታወቃል። በመርሃ ግብሩ ከተሳተፉ ሚኒስትሮች መካከል አስተያየታቸውን የሰጡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር)፥ ባለፉት ዓመታት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሁሉም መስክ መሰረት መጣሉን ተናግረዋል። የደን ሽፋንን በማሳደግ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃን በማጎልበትና የግብርና ምርታማነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ የወጪ ንግድ አቅምን ማስፋት ማስቻሉን ጠቅሰዋል። በሁሉም የልማት መስኮች የኢኮኖሚ ዕድገትን በማፋጠን ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ኢትዮጵያ እንድታንሰራራ እያደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በመሳተፍ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍም ጥሪ አቅርበዋል። የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፥ አረንጓዴ አሻራ ጤናችን፣ ምግባችን እና ሁሉ ነገራችን ነው ብለዋል። በአረንጓዴ አሻራ ለባህላዊና ዘመናዊ መድሃኒት የሚያገለግሉ ዕጽዋቶች እየተተከሉ መሆኑን ጠቅሰው፥ ይህም የመርሃ ግብሩን ሀገራዊ የጤና ዘርፍ ፋይዳ የላቀ ያደርገዋል ነው ያሉት። መርሃ ግብሩ ምቹና አረንጓዴ አካባቢን በመገንባት ለህብረተሰብ ጤና አጠባበቅ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፥ ሁሉም ህብረተሰብ በችግኝ ተከላው የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት ገልጸዋል። የፍትሕ ሚኒስትር ሀና አርዓያ ሥላሴ፥ ኢትዮጵያውያን በአረንጓዴ ልማት አኩሪ የሆነ ባህል አለን ሲሉ ገልጸዋል። ይህን መልካም ባህል ማስቀጠል እንደሚገባ በመግለጽ፥ ኢትዮጵያን አረንጓዴ በማልበስ ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ ሁሉም ጥረቱን ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተይዟል።
በሲዳማ ክልል የአረንጓዴ አሻራ ልማት የአየር ንብረት ለውጥን ከመጠበቅ ባለፈ ምርታማነትን እያሳደገ ነው
Jun 30, 2025 47
ሀዋሳ፤ ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን ከመጠበቅ ባለፈ ምርታማነትን ማሳደጋቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ደስታ ዛሬ በዳራ ኦቲልቾ ወረዳ ሾይቾ ቀበሌ ተገኝተው የክልሉን የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር አስጀምረዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን በመጠበቅና የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችን አስገኝተዋል። ዛሬ በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የሚተከሉ ችግኞች ለመጪው ትውልድ የሚሻገሩ በመሆኑ ከመትከል ባለፈ በአግባቡ ጸድቀው እንዲያድጉ መንከባከብ ይገባል ብለዋል። ዛሬ ክልል አቀፉ ተከላ የተጀመረበት ቦታ ከዚህ ቀደም የተራቆተ እንደነበረና በተደጋጋሚ በተሰራው የአረንጓዴ ልማት ሥራ ውጤት የተመዘገበበት በመሆኑ ወደሌሎች አካባቢዎችም ማስፋት ይገባል ብለዋል። በክልሉ በክረምት ወራት የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል ዝግጅት መደረጉን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ የክልሉ ህዝብ በልማት ሥራው በተደራጀ መንገድ እንዲሳተፍም ጥሪ አቅርበዋል። በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ፣ የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት አልፏል- የሕንድ ፖሊስ
Jun 12, 2025 467
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የ204 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቷ ፖሊስ አስታወቀ። በሕንድ 242 መንገደኞችን ይዞ በህንድ ሰሜን ምዕራባዊ ክፍል አህመዳባድ ከተማ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ለንደን ጋትዊክ ለማምራት በተነሳበት ቅፅበት በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ተከስክሷል። በቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ውስጥ 169 ህንዳውያን፣ 53 የብሪታኒያ ዜጎች፣ 7 ፖርቹጋላዊ እና አንድ ካናዳዊ ነበሩ። በአደጋው የተረፈ ሰው ለማግኘት የሚቻልበት እድል እጅጉን የጠበበ ነው ሲል የአህመዳባድ ፖሊስ ኃላፊ ለአሶሲዬትድ ፕሬስ ገልጾ ነበር። ይሁንና ማምሻውን በወጣ መረጃ የ40 ዓመት የህንድ እና ብሪታኒያዊ ጥምር ዜግነት ያለው ቪሽዋሽ ኩማር ራሜሽ ከአደጋው መትረፉ ተጠቁሟል። እስከ አሁን የ204 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የአውሮፕላኑ አካል የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ላይ ወድቆ ቢያንስ አምስት የህክምና ተማሪዎች መሞታቸውን እና 50 ገደማ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት አደጋው ቃል ከሚገልጸው በላይ ልብ የሚሰብር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በአደጋው ለተጎዱ በሙሉ ልባዊ ሀዘናቸውን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ኮሚሽኑ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ ይሰራል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 12, 2025 1058
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት ማስፈን ዋንኛ የፖሊሲ የትኩረት አቅጣጫው በማድረግ እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ዛሬ ትውውቅ እና ቆይታ አድርገዋል። ሊቀ-መንበሩ በስልጣን ጊዜያቸው ሊያሳኳቸው ስላቀዷቸው ተቋማዊ ግቦችና ቅድሚያ ሰጥተው ለመፈጸም ያሳቧቸውን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ አስተዳደር በሰላም፣ ደህንነት፣ ልማትና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሰላምና ደህንነት የኮሚሽኑ ዋንኛ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመልክተዋል። ኢ-ሕገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች በአፍሪካ መረጋጋት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት መሰል ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም ሰላምን በማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን በማረጋገጥ የህብረቱ አባል ሀገራትን ሉዓላዊነት እና ደህንነት መጠበቅ ላይ አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት። ሊቀ-መንበሩ በገለጻቸው ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካን ድምጽ የበለጠ ለማጉላት እንደሚሻ ገልጸዋል። በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ የአፍሪካ ህብረትን ሚና ማጠናከር ቁልፍ ግብ መሆኑን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግበት በጽኑ ሁኔታ እንደሚሟገት አመልክተዋል። ሊቀ-መንበሩ የፀጥታው ምክር ቤት አሁናዊ መዋቅር የታሪክ ኢ-ፍትሃዊነት በማለት የገለጹት ሲሆን አፍሪካ በዓለም አስተዳደር የሚገባትን ትክክለኛ ስፍራ በሚገልጽ ሁኔታ ምክር ቤቱ ማሻሻያ ሊደርግበት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚና ሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት በአፍሪካ ፈጠራ እና ዘላቂ ልማትን ማሳለጥ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ በማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ወጥነት ባለው መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ሊቀ-መንበሩ በአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል አማካኝነት ወረርሽኝን የመከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱንም አንስተዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አዲሱ ሊቀ-መንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ በቀጣይ ከሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር በየሶስት ወር ጊዜ ቆይታ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል። በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መሐመድ አሊ ዩሱፍ ሙሳ ፋቂ ማህማትን በመተካት የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው።
ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ያላትን የአፈጻጸም ሪፖርቶች ማቅረብ ጀመረች
May 10, 2025 754
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ በፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው። በጋምቢያ ባንጁል የአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት እየተካሔደ ባለው ስብሰባ ላይ በአፍሪካ የሰዎችና ህዝቦች መብቶች ቻርተር (ባንጁል ቻርተር) ወቅታዊ የኢትዮጵያ አፈጻፀምና በአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) መነሻ ወቅታዊ አፈጻፀም ላይ ልኡኩ ሪፖርቶችን ማቅረብ ጀምሯል። ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በሪፖርት ዘመኑ በቻርተሩና ፕሮቶኮሉ መሰረት ያሉባትን ግዴታዎች ለመወጣትና የሰብአዊ መብቶችን ከማስጠበቅ አንጻር የተወሰዱ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን የሚመለከቱ ለውጦች ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል። በኮሚሽኑ መርሃ-ግብር መሰረትም ሪፖርቱን ተከትሎ ከኮሚሽነሮች ለተነሱ ጥያቄዎች ኢትዮጵያ በልዑካን ቡድኑ አማካኝነት ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2017 ምላሾችን ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል። መድረኩ ኢትዮጵያ በባንጁል ቻርተር እና በማፑቶ ፕሮቶኮል ስምምነቶች መሰረት በአገሪቱ የሰብዓዊ መብቶችን እና የፆታ እኩልነትን ለማጎልበት ያላትን ቁርጠኝነት የምታሳይበት እንደሆነም ተገልጿል።
በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
Apr 23, 2025 1376
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦በዛሬው እለት በቱርኪዬ ኢስታንቡል በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እንደ አናዶሉ የዜና ወኪል ዘገባ ዛሬ ቀትር ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የኢስታንቡል እና ጎረቤት አካባቢ ነዋሪዎች በፍርሃት የመኖሪያ ህንጻቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። በሌላም በኩል ረፋዱ ላይ በኢስታምቡል አቅራቢያ የባህር ዳርቻ ቡዩኪክሚ የተባለ ስፍራ ላይ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አናዶሉ የዜና ወኪል የሃገሪቱን የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣን ጠቅሶ ዘግቧል። በአደጋው ምንም የተመዘገበ ጉዳት እንዳልተከሰተ የጠቀሰው ዘገባው ነዋሪዎች የዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ሁኔታ ሲገጥም የተጎዱ ሕንጻዎች ውስጥ እንዳይገቡ የግድ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ተሽከርካሪዎችን እንዳይጠቀሙና ሌሎች የጥንቃቄ መልዕክቶችን ባለስልጣኑ ማስተላለፉም ተገልጿል። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውንና ለዜጎችም መልካም ሁኔታ እንዲገጥማቸው መመኘታቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ከሃገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መቆጣጠር ባለስልጣንና ከሚመለከታቸው አካላት መረጃዎችን በመቀበል በቅርበት እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል።
ሐተታዎች
ውበትና ትጋት በህንድ
Jun 27, 2025 188
በቤተልሄም ባህሩ (ኢዜአ) በልጅነቴ እያየሁ ያደግኳቸው አብዛኛዎቹ ፊልሞች የህንድ ናቸው። ይህ ደግሞ ከአገራችን አርቲስቶች በላይ የህንድ የፊልም ተዋንያኑን ስም ለመለየት አስችሎኛል። የህፃንነት ዘመኔን የሚያስታውሱኝን ፊልሞች ከትዝታ ማህደሬ እያወጣሁ ከመተረክ በስተቀር ህንድን የማይበት አጋጣሚ ይኖራል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚያን በህንድ ፊልም የማደንቃቸውን የምደመምባቸውን የህንዳውያንን ሶስት ከተሞች ለመጎብኘት ከተመረጡ ከሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ የተውጣጡ ጋዜጠኞች መካከል መሆን ድንገቴ ሆነብኝ። እኔም ብቻ ሳይሆን አብዛኛዎቹ የጋዜጠኞች ልዑካን ህንድ ከልጅነት ትዝታቸው ጋር የተሳሰረ አንዳች ነገር አለው። ህንድ በፊልሞቿ የሚያቋት ስለመሆኑ ጉብኝቱን ተከትሎ በተካሄደው በዶርሻን የቴሌቪዥን ጣቢያ ውይይት ላይ ሲያነሱ ሰምቻለሁ። በዓለም ላይ በህዝብ ብዛቷ ቀዳሚዋ ህንድ የብዝሃ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት አገር ናት። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኪነ ጥበብ ስራዎቿ በዓለም ላይ ትታወቃለች። ለጉብኝት ከተጋበዙት የጋዜጠኞች ቡድን መካከል አባል ሆኜ በዴልሂ፣ አግራና ባንጋሎሩ ከተሞች በተጓዝንባቸው ስፍራዎች ሁሉ የታዘብኩት ህንዳዊያን በስራና ትጋት ላይ መሆናቸውን ነው። ሁሉም ነገውን ለማሳመር የራሱን ድርሻ ለማኖር፤ ለሀገሩ እድገትና ልማት አሻራውን ለማኖር እንደሚታትር መረዳት ይቻላል። ባረፍንበት ሆቴል ያሉ ሰራተኞች፣ በገበያ ስፍራ የምናገኛቸው ሰዎች እንዲሁም በጎበኘናቸው ስፍራዎች ያሉ ሰዎች ሁሉ ለሀገራቸው እድገትና ልማት ብሎም ነጋቸውን ለማሳመር የራሳቸውን ድርሻ ለማኖር ይታትራሉ። አብሬ ከነበርኳቸው ጋዜጠኞች ጋር ስናወጋ የምናነሳው በከተማዋ በተጓዝንባቸው ጎዳናዎች የምናየው የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በየተቋማት የሚታትሩ ሰራተኞች እንዲሁም በንግድ የተሰማሩ ሰዎች ደፋ ቀና ማለት ለአገር የሚያደርጉትን ልፋት ነው። አንድ ቀን በጋራ ሆነን ወደገበያ ስፍራ ስናቀና በፍጥነት የሚደርሱ ምግቦች ተመግበው ለመሄድ የሚፋጠኑ ህንዳውያንን ያየ የጋዜጠኛ ቡድኑ አባል መሰል ልምድና ጊዜ አጠቃቀም በአፍሪካም ሊለመድ የሚገባውና የአህጉራችንን የስራ ባህልና እድገት የሚያረጋግጥ መሆኑን የገለጸበት ሁኔታ ለአገሬው ህዝብ ታታሪነት እንደማሳያ አድርጌ ላነሳው ወደድኩ። በሄድንባቸው አካባቢዎች ሁሉ አዲስ ሰው ሲያዩ ለማገዝ አና ስለነገሮች ለማስረዳት የሚፈጥኑ ዜጎችን ተመልክቻለሁ። በተጓዝኩባቸው ከተማዎች ያየኋቸውን ስፍራዎች ከማስታወሻዬ እየነቀስኩ ለእናንተ ላካፍል ወደድኩ። በቅድሚያ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የስድስት ሰዓት ተኩል በረራ በማድረግ የመጀመሪያ መዳረሻ ያደረግናትን ዴልሂን እንቃኛለን። ዴልሂ- ታሪካዊ ህንፃዎችን ከአዲሶቹ ጋር አጣምራ የያዘች ጥንታዊ ስልጣኔን ከዘመናዊው ጋር አዋህዳ የምታንፀባርቅ ከተማ ናት። በከተማዋ በተዘዋወርንባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከጎዳናዎቿ እስከ ህንፃዎቿ ምድረ ግቢ ድረስ በእፅዋት የተሞላችና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት የሰጠች መሆኗን በግልፅ ያሳየች ከተማ ናት። በዴልሂ ብቻም ሳይሆን በተዘዋወርንባቸው በሶስቱም ከተሞች ጎዳና ስንጓዝ ያየናቸው ግዙፍ ዛፎች ትናንት አገሪቷ ለእፅዋት የሰጠችው ትኩረት ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት እየተከናወነ ያለው ተግባር እንዲሁም በኮሪደር ልማት ከተሞችን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አሁን ላይ ካመጡት ለውጥ ባለፈ ለወደፊት የሚኖራቸውንም መዳረሻ አሻግሬ ለማየት አስችሎኛል። አሰላሳዮቹ - በዴልሂ ቆይታችን በመጀመሪያ ያቀናነው ጥናቶችን በመስራትና ውይይቶችን በማድረግ በኩል አበርክቶ እያደረገ ያለውን ኦብዘርቨር ሪሰርች ፋውንዴሽን የተሰኘ አሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን (ቲንክ ታንክ ግሩፕ) ነው። ተቋሙ በአገር ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የመስራት ተልዕኮን አንግቦ የተነሳ ቢሆንም አሁን ላይ ከኢኮኖሚና እድገት ባለፈ በኢነርጂ፣ አካባቢ፣ በደህንነትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑና ለውሳኔ የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በማመንጨት የአገሪቷን ህዝብና መንግስት እያገዘ ይገኛል። ከተቋሙ አባላት ጋር ባደረግነው ቆይታ ለራስ ችግር የራስ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ስለመሆኑ በአጽንኦት አንስተዋል። የአፍሪካ አገራት ትብብር የአህጉሪቷን ልዕልና ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑም ተነስቷል። የአሰላሳይና ሃሳብ አመንጪዎች ቡድን አባላቱ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ጨርሰን በቀጣይ ያመራነው በህንድ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ባሉ አገራት ጭምር በባቡር መንገድ መሰረተ ልማት ላይ አሻራ እያኖረ ወዳለው ራይትስ ወደተሰኘው ተቋም ነው። የህንድ የባቡር መንገድ የቴክኒካልና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት (Rail India Technical and Economic Service) የተሰኘው ይህ ተቋም ላለፉት 51 ዓመታት በባቡር መንገድ ጠበብቶች አማካኝነት በህንድና በመላው ዓለም ባሉ 62 አገራት በዘርፉ ሲሰራ ቆይቷል። የእጅ ጥበብ ገበያ - ቀጣይ መዳረሻችን ደግሞ ዲል ሃት ኢና የተሰኘው የባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች እንዲሁም የቤት ማስዋቢያዎች መገኛ ወደ ሆነው ገበያ ነው። ገበያው ባይገበዩበትም ዞረው እንዲቃኙ የሚያስገድድ አንዳች ድምቀትን የተላበሰ መሆኑን ባደረኩት ቆይታ አስተውያለሁ። የንግድ ማህበር የሆነው የህንድ ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ሲአይ አይ) በዴልሂ ቆይታችን ካየናቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው። ተቋሙ የንግድ፣ ፖለቲካ፣ የትምህርትና የሲቪል ማህበረሰብ አመራር አባላትን በጋራ በማሰለፍ ዓለም አቀፍና የኢንዱስትሪ አጀንዳዎችን እንዲቀርፁ የሚሰራ ነው። አደጋን የሚቋቋም መሰረተ ልማት ጥምረት (CDRI) በነበረን ቆይታ ጥምረቱ ከአገራት፣ ከተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችና መርሃግብሮች፣ ከፋይናንስና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር የአየር ንብረትና የአደጋ ስጋትን የሚቋቋም መሰረተ ልማት አስተዳደር ላይ እየሰራ መሆኑን ተገንዝበናል። ጥምረቱ የአደጋ ምላሽና መልሶ ማቋቋም፣ በተቋማትና ህብረተሰብ አቅም ግንባታ ድጋፍ ላይ ይሰራል። ጥምረቱ 46 አባል አገራትና ስምንት አጋር ድርጅቶች ያሉበት ሲሆን፤ አገራትና ዓለም አቀፍ አካላትን በማስተባበር የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርግ የጥናትና ፈጠራዎች ውጤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትም ነው። የህንድ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዴልሂ(IIT Delhi) ሌላው የጉብኝት መዳረሻችን ነበር። ኢንስቲትዩቱ በኢንጂነሪንግና ሳይንስ ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በርካታ ሰዎችን አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ስራ ፈጣሪዎችን ማፍራት የቻለ ተቋም መሆኑን መገንዘብ ችለናል። ብሄራዊ ሙዝየም - በኒው ዴልሂ የሚገኘው የህንድ ብሄራዊ ሙዚየም በአገሪቱ ያለ ትልቁ ሙዚየም ሲሆን፤ በጉብኝታችን ወቅት ለዘመናት የቆየች ቅሪተ አካልን ጨምሮ፣ የተለያዩ የጥበብ ውጤቶችና የታሪክ አሻራ ማሳያ ስራዎችን ቀርበው ይጎበኙበታል። በዴልሂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተደረገልን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባባልና ውይይት ህንድና አፍሪካ የጠነከረ ቁርኝት ያላቸውና በንግድ አጋርነትት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆኑ ተመላክቷል። በተደረገልን ገለፃ ህንድና የአፍሪካ የንግድ መጠን 100 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ነው። ህንድ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ ፋርማሲዩቲካል ፣ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ፣ ማዕድን እና የባንክ ዘርፎችን ያላት የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ወደ 75 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መድረሱም ተገልጿል። ኢትዮጵያም ከህንድ ጋር ለዘመናት የዘለቀ ወዳጅነት ያላትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷም ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተነስቷል። ሁለቱ አገራት ያላቸው ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በባህል ትስስር ጭምርም የተጋመደ መሆኑ ተመላክቷል። ለወደፊቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ካሉ አገራት ጋር የምታደርገው ትብብርና ወዳጅነት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑም ተነስቷል። አግራ- የህንድ ታሪክ፣ ባህልና ኪነ ህንፃ መገለጫ በሆነችው አግራ ተገኝተን የጎበኘነው ህንድ ስትነሳ ስሙ ተያይዞ የሚነሳውን ታጅ መሃልን ነው። ታጅ መሃል በእምነ በረድ የተሰራ ውብ ኪነ ህንፃ ሲሆን፤ ንጉስ ሻህ ጃሃን ከሌሎች ሚስቶቹ ሁሉ አስበልጦ ለሚወዳት ሚስቱ ሙምታዝ መሀል ክብር ሲል የገነባው ድንቅ የእጅ ስራ ውጤት ነው። ታጅ መሃልን ስንጎበኝ የነበረው ሙቀት ሀይለኛ ቢሆንም ላባችን እየተንቆረቆረ ንጉሱ ለፋርስ ልዕልቷ ሚስቱ የነበረውን ፍቅር በተመለከተ በአስጎብኚያችን የሚሰጠንን ማብራሪያ ስናደምጥና የፍቅር ሃያልነትን ስናደንቅ ነበር። በዴልሂ ከጉብኝታችን ባሻገር በኢንዲያን ጌትና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በከተማዋ ጎዳናዎች ተዘዋውረን የህዝቡን ፍቅርና ተባባሪነት አይተናል። በተለይ ቦታ የጠፋን መሄድ ያሰብንበት ቦታ እንዳለ የሚያመላክት ፍንጭ በግርታችን ያስተዋሉ ከመሰላቸው "እዚህ መሄድ ፈልገህ ነው ይህን እዚህ ማግኘት ትችላለህ" የሚል ጥቁምታ በመስጠት እንግዳ ተቀባይነትና ሰው አክባሪነታቸውን ይገልፁልሃል። በዴልሂና አግራ የነበረንን ጉብኝትና ትዝታ እያሰላሰልን ቀጣይ መዳረሻ ያደረግናት ባንጋሎሩ ከተማን ነው። ባንጋሎሩ ቀጣይ ትረካችን ይሆናል።
ስራዋን በውጤታማነት በማስቀጠል ለሌሎች ወጣቶችም መትረፍ የቻለችው ወጣት
May 22, 2025 783
ብርሃኑ ፍቃዱ - ከሰቆጣ ኢዜአ በ2013 ዓ.ም የልብስ ስፌት ስራ የጀመረችው ወጣት ማህደር አስማረ፤ ነዋሪቷ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ ሰቆጣ ከተማ ነው። ስራዋን በውጤታማነት የቀጠለችው ወጣት ከአንድ የልብስ ስፌት መኪና ተነስታ ወደ ሶስት የልብስ ስፌት መኪና የደረሰች ሲሆን ካፒታሏንም ከዓመት ዓመት በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ስራዋን ለመጀመርም ባጠራቀመችው አነስተኛ ገንዘብ ቤት ተከራይታ ነበር። ከልብስ ስፌት መኪናው በተጨማሪ የሌዘርና የጥልፍ ማሽኖችን በማስመጣት የፋሽንና ዲዛይን ስራና ማሰልጠኛ ማዕከል በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች መትረፍ የቻለችበትን አቅም ገንብታለች። የማሰልጠኛ ማዕከሉን ለመክፈት እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ማድረጓን የገለፀችው ወጣት ማህደር፤ 30 ተማሪዎችን ተቀብላ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የምዝገባና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቃለች። "ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ ከመስራት ውጪ ሴትነቴም ሆነ ሌላ ምንም የሚያግደኝ ነገር የለም" የምትለው ወጣት ማህደር ፤ የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከልን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የጨርቃ ጨርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት አቅዳ እየሰራች መሆኑን ገልፃለች። ወጣት መሰረት ጌታቸው በማህደር የልብስ ስፌትና የፋሽንና ዲዛይን ማሰልጠኛ ማዕከል ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የስራ እድል ተጠቃሚ ሆናለች። ከድርጅቱ በቂ የልብስ ስፌት ሙያ፣ ልምድና እውቀት መቅሰሟንና ለዚህም ማህደር እውቀቷንና ልምዷን ሳትሰስት በማከፈሏ ብቁ ሰራተኛ እንድትሆን አድርጋታለች ። የማሰልጠኛ ማዕከሉ በከተማዋ መከፈቱ በተለይም ሴቶችና ወጣቶችን በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት በመሆን ሰርተው የሚለወጡበት እድል የከፈተ ነው በማለት ትገልጻለች። ከወጣት ማህደር ጊዜን በአግባቡ መጠቀምና ጠንክሮ መስራትንና ቁርጠኝነትን ትምህርት ወስጃለሁ ያለችው ወጣት መሰረት ፤ በልብስ ስፌት ዘርፍ ላይም ውጤታማ ለመሆን እየተጋች መሆኑን ትናግራለች። የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ዲያቆን ኪዳነ ማርያም ገብረህይወት፤ ወጣቶች የአካባቢያቸውን ፀጋ ለይተው ከተንቀሳቀሱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ወጣት ማህደር ትልቅ አርአያ ናት ይላሉ። ለአብነትም እንደ ወጣት ማህደር ያሉ ታታሪ ወጣቶችን በስፋት ለማፍራት በስራ እድል ፈጠራ ላይ በማተኮር እየተሰራ እንደሚገኝ ያስረዳሉ። የወጣቷን አርአያነት ለማስፋት በቀጣይ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ እንደሚያበረታቱ አረጋግጠዋል። ወጣቶች በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በባለፉት ወራት ለ11 ሺህ ሰዎች የስራ እድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውንም አውስተዋል።
የኢትዮጵያ የእናቶች ሞትን ምጣኔ ቅነሳ ስኬቶች እና ቀሪ የቤት ስራዎች
May 13, 2025 893
የዓለም የጤና ድርጅት (ደብሊውኤችኦ) የ2025 ዓለም የጤና ቀንን እ.አ.አ አፕሪል 7, 2025 አክብሯል። የዘንድሮው ዓመት የቀኑ መሪ ሀሳብ “ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ፣ ለመጻኢው ብሩህ ጊዜ” የሚል ነው። የዓለም የጤና ጉዳዮች የበላይ አካል የሆነው ደብሊውኤችኦ መሪ ሀሳቡን መሰረተ በማድረግ ዓመቱን ሙሉ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ አስመልክቶ ንቅናቄ ያደርጋል። በኢትዮጵያም የዓለም የጤና ቀን ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ፓርክ “ ከቃል ያለፈ የተግባር ምላሽ” በተሰኘ ሁነት ተከብሯል። በአከባበሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች፣ የጤና ሰራተኞች፣ ቤተሰቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። የጤና ሚኒስቴር፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል። በእንጦጦ ፓርክ የነበረው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ሁነቱን አስቦ ከመዋል ያለፈ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት ኢትዮጵያ ለእናቶች እና ህጻናት ሞት ቅነሳ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳየቷን ገልጿል። የእናቶች እና ህጻናት ጤና የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰብዓዊ መብት፣ የማህበራዊ ልማት እና የብሔራዊ ልማት ጉዳይም ጭምር እንደሆነ የዘንድሮው የዓለም የጤና ቀን አከባበር ያሳየ እንደሆነ ተገልጿል። እንደ ዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ከ100 ሺህ እናቶች መካከል ከ400 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጡ ነበር። ኢትዮጵያ ይሄን አሃዝ በመቀየር የራሷን ታሪክ ፅፋለች። በአሁኑ ሰዓት የእናቶች ሞት ምጣኔ ከ100 ሺህ እናቶች ወደ 195 ዝቅ ብሏል። ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ኢትዮጵያ በጤናው ስርዓት፣ የሰው ኃይል ስልጠና እና የአገልግሎት አቅርቦት ላይ እያደረገች ያለውን ዘላቂ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳይ ድርጅቱ ገልጿል። ይሁንና አሁንም በኢትዮጵያ በየአመቱ በአማካይ 8 ሺህ ገደማ እናቶች በወሊድና ከወሊድ ጋር በተገናኘ ችግር እንደሚሞቱ መረጃው ያመለክታል። በእናቶች እና ህጻናት ጤና ጥበቃ እየተደረገው ያለው ዓመታዊ ንቅናቄ ለለውጦች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ቀሪ የቤት ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባ የሚያመላክት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰው ኃይል ስልጠናን በማስፋት፣ የእናቶች እና ህጻናት ክብካቤን ማሻሻል፣ በዲጂታል መሳሪያዎች አማካኝነት የአገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ላይ መልካም ስራዎች ቢያከናውንም አሁንም የአገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ድርጅቱ አሳስቧል። የጤና መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ቁጥርን መጨመር ሌሎች ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው ብሏል። የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት ቅኝትና ምላሽ ስርዓትን ማጠናከር ሌላኛው በድርጅቱ የቀረበ ምክር ሀሳብ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ቤጆይ ናምቢያር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በማደግ ላይ በሚገኙ ሀገራት ያለው የእናቶች እና ህጻናት ሞት አሳሳቢ እንደሆነና ጠንካራ ምላሽ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። በዘላቂ ልማት ግቦች እ.አ.አ በ2030 ከ100 ሺህ እናቶች የሚሞቱን ወደ 70 ዝቅ የማድረግ ግብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራት ለማሳካት እየሄዱበት ያለው ርቀት አመርቂ አለመሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከተቀመጠው ግብ አንጻር ብዙ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ይሁንና ኢትዮጵያ በዓለም የፋይናንስ ፈተናዎች እና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በግልጽ ያሳየች ሀገር መሆኗ ተገልጿል። ዓለም በተግባር የታገዘ ምላሽ ከሰጠ መከላከል የሚቻሉ የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ሊሳካ የማይችል ህልም አይደለም። ከእንጦጦ ፓርክ ጎዳናዎች አንስቶ በሀገሪቷ ክፍሎች በሚገኙ የጤና ማዕከላት የእናቶች እና ህጻናትን ሞትን ለመቀነስ የሚወሰዱ እያንዳንዱ እርምጃዎች የወደፊቱን የዓለም መጻኢ ጊዜ ብሩህ የማድረግን ራዕይን የሚያሳካ ነው ሲል የዓለም የጤና ድርጅት ጽሁፉን ቋጭቷል።
ቱሪዝሟ እያደገ የመጣው፣በባህላዊ ምግቦቿ እና ቡናዋ ዓለም አቀፍ እውቅና የተቸራት ኢትዮጵያ
May 11, 2025 724
በባህላዊ ታሪኳ እና ልዩ በሆኑ የምግብ አዘገጃጀቶች የምትታወቀው ኢትዮጵያ የበለጠ የዓለምን ትኩረት እየሳበች ትገኛለች። የናይጄሪያው ቢዝነስ ደይ ጋዜጣ ጋዜጠኛ ቺሶም ማይክል በጋዜጣው ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ብዙዎች በአፍሪካ ምርጡ ምግብ እና በዓለም ላይ ምርጡ ቡና ብለው የሚናገርላት ሀገር ብትሆንም አገሪቷ አሁንም ከሌሎች የአህጉሪቱ መዳረሻዎች ጋር ስትነጻጸር በአንፃራዊነት ጥቂት ቱሪስቶችን የምታስተናግድ ሀገር እንደሆነች ይገልጻል። ሞሮኮ እ.አ.አ በ2024 17 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቱሪስቶችን ስትቀበል ኬንያ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ጎብኚዎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያም የበርካታ ቱሪስቶች መዳረሻ የመሆን ጊዜዋ እየመጣ ይመስላል። የተባበሩት መንግስታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት (ዩኤንደብሊውቲኦ) በቅርቡ ባወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው እስከ 2024 ባለው አምስት ዓመት ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ አለም አቀፍ ቱሪስቶች በ40 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። 54ቱንም የአፍሪካ ሀገራት የጎበኙ አንድ ተጓዥ ኢትዮጵያን ሁለተኛ የቱሪዝም ተመራጭ አድርገውታል። "ለዚች ሀገር በጣም የተለየ ነገር ነው ያለኝ ብዙ ጥሩ የተፈጥሮ ቦታዎች አሏት" ብሏል። ይህም የኢትዮጵያ መንግስት ቱሪዝምን የኢኮኖሚያዊ እድገት ቁልፍ አካል ለማድረግ ያሳየው ቁርጠኝነት እንደሆነ ጋዜጠኛው ይገልጻል። በዩቲዩብ ላይ ከ5 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያለው የቱሪዝም ይዘት ላይ ድሪው ቢንስኪ ይህንኑ ሀሳብ ይጋራል። “ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ምርጥ ምግብ አላት። እንጀራ በጣም ጣፋጭ ነው በዓለም ሌላ ቦታ እንደዚህ ያለ ምግብ የለም። በአፍሪካ ምርጥ ምግብ፣ በዓለም ምርጥ ቡና ያለው እዚህ ሀገር ነው።” "እንጀራ ከጤፍ የተሰራ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ምግብ ውስጥ በጣም ዋና አካል ነው። እንጀራው ከብዙ ምግቦች እና ቅመሞች ጋር ይቀርባል።" ሲል ገልጿል። ኢትዮጵያዊያን የሚታወቁት በምግብ እና ቡና ብቻ አይደለም። ቱሪስቶች በኢትዮጵያ የተፈጥሮ እና ታሪካዊ መዳረሻዎች በጣም ይማረካሉ። በድንጋይ ከተቀረጹ የላሊበላ ውቅር አብያተ ቤተክርስቲያናት በጣም የሚጎበኙ የቱሪዝም መስህብ ነው። በጥልቅ ስምጥ ሸለቆ የታጀበው የሰሜን ተራሮች ለሰዎች ምቹ የእረፍት ጊዜ የሚሰጡ ናቸው። መዲናዋ አዲስ አበባ የባህል እና የምግብ ሁነቶች ማዕከል ናት። የኢትዮጵያ የቱሪዝም ልማት አካሄድ ቅርስ፣ መልክዐ ምድሮች እና ባህላዊ ልምዶችን ጨምሮ የተለያዩ መዳረሻዎችን ማስተዋወቅ ላይ ያተኮረ ነው። ካላት የቱሪዝም መዳረሻ አንጻር በኢትዮጵያ ብዙ ጎብኚዎች ባይኖሩም ያሏትን እድሎች በማስተዋወቅ ተደራሽነቷን እያሰፋች ነው። ልዩ ማንነት ያለው እና ጥልቅ ታሪክ ያላትን ኢትዮጵያን መጎብኘት ለሚሹ ሰፊ የቱሪዝም እድሎችን የምታቀርብ ሀገር ናት ይላል ጋዜጠኛው። በኢትዮጵያ ቱሪዝም እየጨመረ ብዙ ጎብኚዎች በምግቧ፣ ቡናዋ እና ታሪካዊ መዳረሻዎቿ እየተሳቡ ነው። በኢትዮጵያ ባህል እና የምግብ አሰራር ከዕለት ተዕለት የዜጎች ህይወት የተቆራኘባት ሀገር ናት። ኢትዮጵያ የተለየ ነገር ማቅረቧን ቀጥላለች። የቱሪዝም ሀብቶቿ ገና ያልተነካ ነው ኢትዮጵያ የወደፊት የዘርፉ እድገት አቅም ትልቅ ነው በማለት ጋዜጠኛ ቺሶም ጽሁፉን ቋጭቷል።
ትንታኔዎች
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 2948
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት
Dec 16, 2024 2508
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ቀጣና ዘለል አንድምታ ያለው የአንካራው ስምምነት
Dec 13, 2024 2728
የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ አንድምታ ከቀንዱ ሀገራት የተሻገረ ነው። የቀጣናው ሀገራት ትስስርና ትብብርም እንደዚያው። በነዚህ ሀገራት መካከል የሚፈጠር መቃረን የሚያሳድረው ተጽዕኖም አድማስ ዘለል ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማልያ መካከል ተፈጥሮ የነበረው የግንኙነት መሻከር ከሁለቱ ሀገራት ባሻገር በቀጣናው ስውርና ገሀድ ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኃይሎችን ያሳሰበና ያስጨነቀ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው። በቱርክዬ ርዕሰ ከተማ አንካራ የተደረሰው የኢትዮ-ሶማልያ ሥምምነት ግን ለበርካቶች እፎይታን ይዞ መጥቷል። ከኢትዮጵያና ሶማልያ ጋር መልካም ወዳጅነት ያላት ቱርክዬ የሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት ከጀመረች ውላ አድራለች። ምንም እንኳ ጥረትና ድካሟ በተደጋጋሚ ሳይሳካ ቢቆይም ካለፈ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በሚኒስትሮች ደረጃ ለማረቅ ተግታለች። በሦስተኛው ዙር በሁለቱ ሀገራት መሪዎች ደረጃ የተደረገው ድርድር ግን ፍሬ አፍርቶላታል። ቱርክዬ እየተገነባ ባለው የብዝሃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ጎልተው እየወጡ ካሉ ኃያላን ሀገራት መካከል አንዷ ናት። በአፍሪካ ውስጥ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነትም እያደገ መምጣቱ ይታወቃል-በተለይ በአፍሪካ ቀንድ። ቱርክዬ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ታሪካዊና ዘርፈ ብዙ ትስስር ጠንካራ የሚባል ነው። ቱርክዬ ከቻይና ቀጥላ በኢትዮጵያ ግዙፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ያፈሰሰች ሀገር ናት። ከኢኮኖሚያዊ ቁርኝቱ ባሻገር ሁለቱ አገራት በፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ጉዳዮች ያላቸው ትብብርም የላቀ ነው። ቱርክዬ ከሶማልያ ጋር ያላት አጋርነትም እየተጠናከረ የመጣ ነው። እናም የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት ለቱርክዬ ሳንካ ነበር። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት አለመግባባት በአንካራው ድርድር ዲፕሎማሲያዊ እልባት ማግኘቱ ለፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ወሳኝ እርምጃ ሆኖላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአንካራ ተገኝተው ያደረጉት ውይይት የቀንዱን ውጥረት አርግቧል። ስምምነቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል። በሶማልያ በኩል ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ዘላቂነት ያለው የባሕር በር የማግኘት መብትን ዕውቅና ለመስጠት እና በዚህ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት መስማማት ችላለች። በተመሳሳይ ኢትዮጵያም የሶማልያን የግዛት አንድነት ለማክበር የነበራትን የቆየ አቋም አጽንታለች። ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ለማካሄድ ተስማምተዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው ኢትዮጵያ በሶማልያ የባሕር ዳርቻ በኩል ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት ዙሪያ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።ይህ የወደብ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም ለምትፈልገው ኢትዮጵያ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያና የሶማልያ ሕዝቦች በቋንቋ፣ በባህል እና በጉርብትና ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰሩ ወንድማማቾች እና እህታማማች ሕዝቦች መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል። ይልቁንስ ሶማልያን ከአሸባሪዎች ለመከላከልና ሠላሟን ለማረጋገጥ ሲባል በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት በከፈሉት መስዋዕትነት ጭምር የተሳሰረ መሆኑን ነው ግልጽ ያደረጉት። ኢትዮጵያ ለጋራ ሠላምና ልማት ከሶማልያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የሶማልያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድም ለዚህ ሀቅ ጠንካራ እማኝነታቸውን ሰጥተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለአገሪቱ ሠላም መጠበቅ ለዓመታት የከፈለውን ዋጋ መቼም አይዘነጋም ሲሉ የሚገባውን ክብር አጎናጽፈውታል። ሶማልያ የኢትዮጵያ እውነተኛ ወዳጅ ሆና ትቀጥላለች ሲሉም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም ሠላምን ለማፅናት በሚያደረጉት ጥረት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። በጥቅሉ የአንካራው የአቋም መግለጫ የሁለቱን አገራት የጋራ አሸናፊነት ያንጸባረቀ ነው። ለዘመናት በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ፈጽሞ የተዘነጋ እና የማይታሰብ ይመስል የነበረውን የኢትዮጵያን የባሕር በር ጉዳይ በድፍረት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ለማድረግ ያስቻለ ነው። የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ከሃገር አልፎ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ትስስር ጭምር ወሳኝ መሆኑ መግባባት የተደረሰበት ሆኗል። በተለያዩ አሰራሮች እና አግባቦች፣ በሠላማዊ መንገድ እና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘላቂ የባሕር በር ሊኖራት እንደሚገባ መግባባት የፈጠረ ነው። ይህን ሥምምነት ዕውን ለማድረግ በዝርዝር ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ድርድሮች በማካሄድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢራዊ ለማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ መግባባት ችለዋል። በዚህ ረገድ ቱርክዬ ሂደቱን ለማሳለጥ እና ለማገዝ ኃላፊነት መውሰዷ ደግሞ ዘላቂነት እንዲኖረው እንደ መልካም ዕድል የሚወሰድ ነው። ኢትዮጵያና ሶማልያ በአንካራ የደረሱት ስምምነት ከአውሮፓ ኅብረት እስከ አፍሪካ ኅብረት እንዲሁም ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) እስከ ተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት አድናቆት የቸሩት ሆኗል። ይህ ስምምነት የሁለት አገራት ስምምነት ብቻ አይደለም። የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካ የመፍጠር ህልም አካልም ጭምር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የውዳሴው መነሻና መድረሻውም ደግሞ ስምምነቱ የአፍሪካ ቀንድን ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ዘላቂ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ወደ አህጉራዊ ትብብር የሚወስድ መሆኑ ነው። በእርግጥም ሥምምነቱ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከመባቱ በፊት ለቀንዱ አገራት የቀረበ ሥጦታ ነው። እናም የአንካራው ስምምነት ከኢትዮጵያና ከሶማልያ ባለፈ አንድምታው ቀጣናውን የተሻገረ በመሆኑ የአፍሪካውያንና የወዳጅ ሀገራት በቅን መንፈስ የተቃኘ ድጋፍ ያሻዋል። ሠላም!
ህዳሴ - በመስዋዕትነት የተገነባ ነገ
Nov 2, 2024 3848
ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ከፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያውያን በጋራ የመቻል ትምህርት ነው። የወል ዕውነታቸው፣ የወል አቅማቸው፣ የጋራ ተስፋቸው በግልጽ የተንጸባረቀበት የአይበገሬነት ምልክት ጭምር ነው። ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን እንዴት በጋራ መገንባት እንደሚችሉ በሚገባ ያሳዩበት ዳግማዊ አድዋ ነው - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ። አድዋ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የተዋደቁበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለኢኮኖሚ ሉአላዊነት የደም ዋጋ የተከፈለበት የትውልዱ የብሄራዊነት ማሳያ ነው። ህዳሴን ዕውን ለማድረግ ኢትዮጵያ ከሴራ ዘመቻዎች እስከ ዛቻና ማስፈራሪያዎች የደረሱ እንቅፋቶችን አልፋለች። በተለይም የግድቡ ግንባታ ወደማይቀበለስበት ደረጃ በደረሰባቸው ያለፉት 6 ዓመታት ፈተናዎቹ በርትተው ነበር። ለህዳሴው ግድብ ግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ተጓጉዘው እንዳይደርሱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት እንዳያመርቱና እንዳያቀርቡ በተለየዩ ቦታዎች ጥቃቶች ይሰነዘሩ ነበር። ቢሆንም ግን የማያባሩ የኢትዮጵያ ጠላቶችን የተንኮል ወጥመዶች በጣጥሶ ለማለፍ ኢትዮጵያውያን አይተኬ ህይወታቸውን ጭምር ገብረው ነገን ዛሬ መስራትን በህዳሴ ዕውን አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሕዳሴ ግድብ አሁን የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ በርካታ መስዋዕትነት መከፈሉን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሁሌም በጋራ የመልማት እሳቤ ማዕከል መሆኗን ገልጸው፤ታላቁ ህዳሴ ግድብም በኢትዮጵያዊያን ብርቱ ልጆች ከአፍሪካ ለአፍሪካ የተሰጠ ገጸ በረከት እንዲሁም ጣፋጭ ፍሬውም ከኢትዮጵያ ባለፈ ለተፋሰሱ አገራትም ብስራት መሆኑን ነው ያስረዱት። የታላቁ የኢትዮጵየ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ አኩሪ ደረጃ ላይ ለመድረስ ኢትዮጵያውያን ከገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀታቸው ባሻገር የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 2283
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 2161
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 3596
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል። በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል። የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
መጣጥፍ
የዋጋ ንረት ምን ማለት ነው?
Jun 30, 2025 56
የዋጋ ንረት በንፅፅር ለምሳሌ አምና 26 በመቶ ዘንድሮ 14 በመቶ ሲሆን ምን ማለት ነው? ለምሳሌ የአንድን የ100 ብር ዕቃ ወስደን ብንመለከት ካቻምና ከነበረበት 100 ብር አምና 126 ብር ሆኖ ነበር ማለት ነው። ስለዚህ የዕቃው ዋጋ በአመት ብር 26 ጨምሯል ማለት ነው። በተመሳሳይ መንገድ አምና 100 ብር ዋጋ ያለው ዕቃ ዘንድሮ 14 በመቶ ካደገ ዘንድሮ 114 ብር ይሆናል ማለት ነው። በዚህ ስሌት የዕቃው ዋጋ ካምና ወደ ዘንድሮ የጨመረው በ14 ብር በመሆኑ አምና ከጨመረበት ብር 26 ጋር ሲነፃፀር ጭማሪው ቀንሷል ማለት ነው። ዋጋን ያየን እንደሆነ ግን 100 ብር የነበረ ዕቃ 114 በመሆኑ ጨመረ እንጂ አልቀነሰም። የዋጋ ንረት ጨመረ የሚባለው ደግሞ ለምሳሌ አምና 26 በመቶ የጨመረው ዘንድሮ 14 በመቶ ሳይሆን 30 በመቶ ቢሆን የጨመረው አምና 100 ብር የነበረው ዕቃ ዘንድሮ 114 ሳይሆን 130 ብር ይሆናል ማለት ነው። ይህ አምና ከጨመረበት የ26 ብር ይበልጣል ማለት ነው። ስለዚህ ካቻምና 100 ብር የነበረው ዕቃ አምና 26 ብር ጨምሮ 126 ከሆነ በኋላ ዘንድሮም 14 ብር ስለጨመረ በቀላል ቀመር ዘንድሮ 140 ብር ሆኗል ማለት ነው። ስለዚህ በሁለት አመታት የዕቃው ዋጋ 40 ብር ጨምሯል። የዕቃው ዋጋ አልቀነሰም በየአመቱ የጨመረበት ምጣኔ ግን ካምና ዘንድሮ ያነሰ ነው። ይህ ነው የዋጋ ንረት ቀነሰ ማለት። ዋጋ ቀነሰ ማለትስ ምን ማለት ነው? ዋጋ ቀነሰ የሚለውን ከማየት በፊት የዋጋ ንረት የለም ማለት ምን እንደሆነ በዛው 100 ብር ዋጋ ባለው ዕቃ እንመልከት። ይህ ባለፈው አመት ብር 100 የነበረ ዕቃ ዘንድሮም እዛው 100 ብር ላይ ቢቆይ የዋጋ ንረት ዜሮ ነው። ስለዚህ የዕቃው ዋጋ አልተለወጠም ማለት ነው። ዋጋ ቀነሰ ማለት ግን የዋጋ ንረት ከዜሮ በታች ይሆናል ማለት ነው። በምሳሌው ለማስረዳት አምና 100 ብር ዋጋ ያለው ዕቃ ዘንድሮ 90 ብር ቢሆን የዋጋ ንረቱ ወይም ለውጡ ከዜሮ በታች 10 በመቶ ነው። በዚህ ግዜ የዋጋ ንረት ቀነሰ ሳይሆን ዋጋ ቀነሰ ይባላል። እነዚህ ሶስቱ የዋጋ ለውጦች ለሸማቾችና ለአምራቾች ምን ማለት ናቸው? ለሸማቾች ከሁሉም የሚመረጠው ዋጋ ሲቀንስ ማለትም 100 ብር የነበረው ዕቃ 90 ብር ሲሆን ነው። በሁለተኛ ደረጃ ተመራጩ ዋጋ ንረት ሳይኖር አምና 100 ብር የነበረው ዕቃ ዘንድሮም ሳይለወጥ በዜሮ ንረት 100 ብር ላይ ሲቆይ ነው። ሶስተኛው የተሻለ አማራጭ አምና 100 ብር የነበረ ዕቃ ዘንድሮ በ26 በመቶ ጨምሮ ብር 126 ከሚሆን በ14 በመቶ ጨምሮ ብር 114 ሲሆን ነው። ይህ ሶሰተኛው አማራጭ በሁለቱም ዋጋ ስለሚጨምር በትንሽ የጨመረው ተመራጭ ይሆናል ማለት ነው። ከአምራቾች አንፃር ሲታይ ከላይ ለሸማቾች የተሻለ አማራጭ በቅደም ተከተል ያስቀምጥነውን ገልብጠው ማንበብ ነው። አሁን ብሔራዊ ባንክ እያለ ያለው የዋጋ ንረት ወይም አመታዊ ጭማሪው ቢበዛ ከ10 በመቶ እንዳይበልጥ የሚረዳ የገንዘብ ፖሊሲ እተገብራለሁ ነው። የባንኩ አላማ የዋጋ ንረት ዜሮ ወይም ከዜሮ በታች እንዲሆን ሳይሆን 1) ከ10 በመቶ በታች እንዲሆን ሲሆን 2) የትረጋጋና ተገማች እንዲሆን ነው። የተረጋጋ ማለት ከወር ወር ወይም ካመት አመት ዋጋ የሚለወጥበት ሁኔታ በጣም የተራራቀ ያልሆነ ማለት ነው። ለምሳሌ ካንዱ ወር ወደ ቀጣይ ወር ጭማሪው 0.5 በመቶ ሆኖ በቀጣይ ወር ደግሞ የ5 በመቶ ጭማሪ ከዚያም በቀጣይ ወር ከዜሮ በታች የ2 በመቶ ወርሃዊ ለውጥ ቢመዘገብ ያልተረጋጋ ወይም ተገማች ያልሆነ የዋጋ ለውጥ አለ ማለት ነው። ሰለዚህ የተረጋጋና ተገማች የዋጋ ለውጥ እንዲኖር ማድረግ የባንኩ ሁለተኛው አላማ ነው ማለት ነው። ብሔራዊ ባንክ በጣም ዝቅተኛ የዋጋ ንረት ወይም ከዜሮ በታች የዋጋ ለውጥ እንዴት ያየዋል ብለን ያየን እንደሆነ ነገሩ እንዲህ ነው። ቅድም ከላይ እንዳየነው የዋጋ ንረት ከሸማቾችና ካአምራቾች አንፃር የሚታየው በተቃራኒ መንገድ ነው። ስለሆነም ምንም እንኳን የዋጋ ንረት በጣም ዝቅተኛ ወይም ከዜሮ በታች ቢሆን ለሸማቾች ጥሩ ቢሆንም አምራቾችን ግን የማያበረታታ ስለሚሆን ማምረት ያቆማሉ ሠራተኛ ይቀንሳሉ አጠቃላይ የኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ይገታና ጭራሽ ከምርት እጥረት የተነሳ የዕቃዎች ዋጋ መናር ይከሰታል ሥራ አጥነት ይበዛል። ስለዚህ መንግስት ሥራ እንዲፈጠር ኢኮኖሚ እንዲነቃቃም ስለሚፈለግ የተረጋጋና ዝቅተኛ ሸማቹን የማይጎዳ አምራቹንም የሚያበረታተ የዋጋ ሁኔታ እንዲኖር ይሰራል ማለት ነው። ለአንድ ኢኮኖሚ ትክክለኛው የዋጋ ንረት ስንት ነው? ይህ ጥያቄ ሊመለስ የሚገባው ግን ከባድ ነው። ይህን ጥያቄ ለመመለለስ ከሚረዱት ሁኔታዎች አንዱ ኢኮኖሚው ያለበት ደረጃ ነው። ምን ማለት ነው በጣም ባደገና የበለጠ የማደግ እድሉ ጠባብ ለሆነ ኢኮኖሚ 1 በመቶ ወይም 2 በመቶ የዋጋ ንረት ከፍተኛ ሊሆን ይችላል። በአንፃሩ ደግሞ ገና የማደግ እምቅ አቅም ላለውና በማደግ ላይ ላለ ሀገር ነጠላ አሃዝ የዋጋ ንረት እንደ ሁኔታው የሚለያይ ሆኖ ተመራጭ ሊሆን ይችላል። ስንት ነው የሚለው ግን በሳይንሳዊ መንገድ መረጋገጥ አለበት። ለምሳሌ የሀገራችንን threshold inflation or optimal inflation level ለማወቅ እኔን ጨምሮ የባንኩ ሠራተኞች በሳይንሳዊ መንገድ ለማወቅ ተሞክሯል። በኔ ጥናት 7 በመቶ ሲሆን በሌሎቹም ከዚሁ ያልራቀ ውጤት እንዳለ አይቻለው የመረጃ አጠቃቀምና የሜቶዶሎጂ ልዩነቱ እንዳለ ሆኖ ማለቴ ነው። ሰለዚህ በነዚህ ጥናት መሰረት ብሔራዊ ባንክ የነጠላ አሃዝ የዋጋ ንረት አላማ አድርጎ መንቀሳቀሱ ትክክለኛ አቅጣጫ ነው ማለት ነው ለኛ ኢኮኖሚ። ለማጠቃለል የዋጋ ንረት ምንነትን በተመለከተ ያለውን ውዥምብር ለማጥራት ይህ አጭር መግለጫ ያግዛል ብዬ እያመንኩ የበለጠ መብራራት ካለበት ወይም ጥያቄ ካለ አንባቢዎች በአስተያየት መስጫው ላይ ማሰቀመጥ ትችላላችሁ። አቶ ፈቃዱ ደግፌ የብሔራዊ ባንክ ም/ገዥ
የሺህ ሀይቆች ምድር
Jun 24, 2025 389
የሺህ ሀይቆች ምድር (በራሔል አበበ) በርካታ መገለጫዎች አሏት። የሺህ ሀይቆች መፍለቂያ። አረንጓዴ ምድር። 75 በመቶ የአገሪቱ ገፀ-ምድር በደን የተሸፈነ። የአምስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ሕዝብ መኖሪያ። በአውሮፓ ከበለጸጉ አገራት አንዷ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለስምንት ተከታታይ ዓመታት በዓለም ቁጥር አንድ የደስተኞች አገር በመባል የተሰየመች ሰሜን አውሮፓዊት አገር - ፊንላንድ። በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋባዥነት በአዲስ አበባ የአገሪቱ ኤምባሲ አስተባባሪነት በቅርቡ ፊንላንድን የመጎብኘት ዕድል አግኝቼ ነበር። በጉብኝቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ የኬኒያ፣ ታንዛኒያ፣ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴኔጋል፤ ሞዛምቢክ እና ዛምቢያ ጋዜጠኞች ተሳትፈናል። የአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ ነው። ምንም እንኳን የትም አገር ስሄድ ቀድሜ መረጃ የማየት ልምድ ቢኖረኝም በመጀመሪያው ዕለት ለእራት ስንወጣ ያየሁት በምሽት ያልተለመደ የፀሐይ ፍካት ግን እራቱ ቁርስ እንዲመስለኝ አድርጓል። ከዚያ በኋላ ለመድሁት። በእርግጥ በአንድ ወቅት በስፔንም ፀሐይ እስከ እኩለ ሌሊት የማትጠልቅበትን ክስተት ተመልክቻለሁ። በፊንላንድ ያየሁት ግን ተለየብኝ። ፀሐይ ፈጽሞ ለጨረቃ ቦታ መልቀቅ አትፈልግም። ምሽቱ የሚደምቀው በመብራት ሳይሆን በፀሐይ ነው። ሌሊቱ ብርሀን ነው። ሰማይ አይጠቁርም። በየዕለቱ ሳይጨልም ይነጋል። በዚህ ወቅት በተለያዩ የአውሮፓና የአሜሪካ አገራት ሰማይ ላይ የሚታየው ሰሜናዊ የቀለማት የብርሀን ፀዳል ሌላው የፊንላንድ መድመቂያ ነው። የሰሜን አውሮፓ/ኖርዲክ አገራት በተፈጥሮ የታደሉ ናቸው። እኔ ደግሞ የተፈጥሮ አድናቂ ነኝ። ያለማጋነን በፊንላንድ ተፈጥሮ ከነክብሯ ተጠብቃ አይቻለሁ። ንጹህ አየሯ የዚህ ውጤት ነው። አድናቆቴ የጀመረው ከኤርፖርት እስካረፍኩበት ሆቴል 15 ኪሎ ሜትር ያህል በመኪና ስንጓዝ የከተማዋን አረንጓዴነትና የምድሪቱን ልምላሜ ስመለከት ነበር። በጉብኝቴም በተግባር አረጋገጥሁ። የአገሪቱ አብዛኛው መሬት በደንና በውሃ ተሸፍኗል። በዋና ከተማዋ ሄልሲንኪና በዙሪያዋ በሚገኙ ውብ ደኖች መሀል ስንጓዝ መሬቱ ለም ስለመሆኑ ዓይን ብቻ ሳይሆን እግርም ምስክር ነው። ሲራመዱ የመሬቱ ምቾትና እንደ ስፖንጅ ስምጥ ስምጥ ማለት ለምነቱን ይናገራል። በሄልሲንኪ ሴኔት እና ካንሳላስቶሪ አደባባዮች እንደእኛዎቹ አራት እና ስድስት ኪሎ አደባባዮች ናቸው። ቤተ-መንግስት፣ ዩኒቨርሲቲ፣ ፓርላማ፣ ቤተ-መጽሐፍት እና ቤተክርስቲያንን አጎራብተው ይዘዋል። የሄልሲንኪ ሕንጻዎች እንደ ሌሎች የአውሮፓ አገራት ውብና የሥነ-ሕንጻ ጥበብ የሚታይባቸው ናቸው። የነዋሪዎች ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ ከተማዋ አልተጨናነቀችም። በአስፋልትና ደረጃውን በጠበቀ ኮብልስቶን የተሰራው የከተማዋ አውራ ጎዳና ከዘመናዊ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ የህዝብ አውቶቡስና የኤሌክትሪክ ባቡር ያስተናግዳል። ለአውሮፓ ከተሞች አዲስ የሆነ ሰው ኮብልስቶኑ የእግረኛ መንገድ መስሎት መሐል የመኪና መንገድ ላይ ሊገኝ ይችላል። እኔም የተረፍሁት እንዲህ አይነቱን የመኪና መንገድ በአንድ ወቅት በኢጣልያ በማየቴ ነበር። የተፈጥሮ ውበት ደምቆ የሚታይባት ፊልናልድ ሲልቨር በርች የተሰኘው ብርማ ቀለም ቅርፊት ያለው ዛፍ እና ቡናማ ድብ ብሔራዊ መለያዎቿ ናቸው። በረጃጅሞቹ ዛፎች መሐል ከእንስሳት ባሻገር ስትሮበሪና እንጉዳይን ጨምሮ ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ዕጽዋት ይገኛሉ። በፊንላንድ ብዙ አይነት የእንጆሪ/ስትሮበሪ ዝርያ አለ። ወቅቱ ፍሬ የሚደርስበት አልነበረም እንጂ ከጫካዎቹ መሐል ገብቶ በተለያዩ የስትሮበሪ ፍሬዎች ቅርጫት ሞልቶ መውጣት የተለመደ መሆኑን ተረድቻለሁ። ፊንላንድ የሺህ ሀይቆች ምድር ተብላም ትሞካሻለች። ለቁጥር የሚያዳግቱ በበርካታ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሀይቆችና የውሀ አካላት ከተፈጥሮ ሀብቶቿ መካከል ናቸው። ለጉብኝት በሄድኩባቸው አካባቢዎች ሁሉ የሚቀርብልኝን ኩልል ያለ ንጹህ የመጠጥ ውሃ በፍቅር ነበር የምጠጣው። ግዴታ ካልሆነ የፋብሪካ ውሃ በፊንላንድ ቦታ የለውም። ንጹህ የተፈጥሮ የምንጭ ውሃ ከቧንቧ ይቀዳል። ጽድት ከማለቱ ጣዕሙ። ፊኒሾች ለባህልና ቅርስ ትልቅ ቦታ አላቸው። በተለይ ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ቁርኝት አስገራሚ ነው። በአብዛኛው አፍሪካ ውስጥ የሚነገር አፈ-ታሪክና ተረት በፊንላንድም ከተፈጥሮ በተለይም ከዛፎችና ከእንስሳት ጋር ተያይዞ ሲተረትና የመድረሻቸው መነሻ እንደሆነ ሲነገር ተደንቄያለሁ። በጉብኝታችን በአንዱ ቀን ኑኪሲኦ ብሔራዊ ፓርክ ሄድን። ይህ ደግሞ እጅግ የተለየ ተፈጥሮን ማያ ስፍራ ነው። በረዣዥም ዛፎች መሐል ካደረግነው ጉዞ በኋላ የቀረበልን ባህላዊው የፊንላንድ የሳውና እና የዋና ግብዣ ነበር። ሳውና የፊንላንድ ባህል ነው። በእንግሊዝኛ ቋንቋ መዝገበ ቃላት ውስጥ ያለ የፊኒሽ ቃል “ሳውና” እንደሆነ ይነገራል። ዛሬ በዓለም ላይ በተለይም በባለኮከብ ሆቴሎች በስፋት የምናገኘው ሳውና መነሻው ፊንላንድ ናት። በርካታ የሳውና ስፍራዎች ከመኖራቸው የተነሳ የሳውና ቁጥር በአገሪቱ ከተመዘገቡ መኪኖች ቁጥር ይበልጣል ይባላል። ግብዣውን ሁላችንም በደስታ ነበር የተቀበልነው። በባህሉ መሰረት ሳውና ውስጥ በቅጠል እየተጠበጠብን ከፍተኛ ሙቀት ሲሰማን ከፊት ለፊት ባለው ቀዝቃዛ የተፈጥሮ ሀይቅ ውስጥ በመግባት ዋና የሚችል ዋኝቶ የማይችል ደግሞ በመነከር ሰውነቱን አቀዝቅዞ እንደገና ወደሳውናው ይመለሳል። የተለየ ነው። የጉብኝቱ ዋና አስተባባሪ አና ላሚላ ትባላለች። የ35 ዓመት የስራ ልምድ ያላት ብስል ዲፕሎማት ናት። በተለያዩ አገራት ፊንላንድን ወክላ ሰርታለች። አሁንም በአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አምባሳደር ነች። ትክክለኛ የኮሙኒኬሽን ሰው ናት። አንቺ ያልኳት በአንቱታ ላርቃት ባለመፈለጌ ነው። ለነገሩ ስትታይም የ35 ዓመት ወጣት እንጂ የ35 ዓመት የስራ ልምድ ያላት አትመስልም። አንድ ቀን አን “መኮንን” በሚለው የአያቴ ስም እየጠራችኝ ስምሽ እኮ የፊኒሽ/የፊንላንድ ነው ይህን ታውቂያለሽ? ከእኛ ጋር ዝምድና ይኖርሽ ይሆን?" አለችኝ ፈገግ ብላ። "ኸረ በፍፁም ኢትዮጵያዊት ነኝ" አልኳት። ትክክል ነበረች። አጭር የፅሁፍ መልዕክት የመለዋወጥ ሀሳብን ለመጀመሪያ ጊዜ ለዓለም ያስተዋወቀው “ማቲ መኮንን” የተባለ ፊንላንዳዊ ኢንጂኒየር ነው። የቴክኖሎጂ ነገር ከተነሳ አብዛኞቻችን ከተንቀሳቃሽ ስልክ ጋር ስንተዋወቅ የያዝነው ኖኪያ የፊንላንድ ምርት ነው። የመኮንንን ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ በተንቀሳቃሽ ስልክ አማካኝነት ለዓለም ይፋ ያደረገውም ኖኪያ ነው። አሁንም ኖኪያ በኔትወርክ ዝርጋታ ጭምር እየሰራ ያለ ግዙፍ የቴሌኮም ተቋም ነው። ኢትዮጵያና ፊንላንድ የረዥም ዓመታት የሁለትዮሽ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው። ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸው 66 ዓመታትን ተሻግሯል። ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ከእርዳታና ትብብር ባሻገር በተለያየ መስክ በጋራ ትሰራለች። በጉብኝቴ ወቅት ያገኘኋቸው የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሌና ቫልቶነን ይህን ግንኙነት የማሳደግ ፍላጎት መኖሩን ነግረውኛል። ከንግድና ኢንቨስትመንት በተጨማሪ ኖኪያን ከመሰሉ ኩባንያዎች ጋር የሚደረግ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና በአገሪቱ ቴክኖሎጂ መዘመኑን የተረዳሁት በአገሪቱ ብሔራዊ የሚዲያ ተቋም ይሌ ያለማንም እርዳታ ዜና ቀርጾ የሚያሰራጭ ሰው አልባ ሮቦትድ የስቱዲዮ ቴክኖሎጂ ስመለከት ነበር። ፊንላንድ በትምሕርት ጥራትም ስሟ በቀዳሚነት ይነሳል። በአገሪቱ ከ800 በላይ፤ በመዲናዋ ደግሞ 40 የሚጠጉ ቤተ-መጻሕፍት አሉ። ከአገሪቱ ፓርላማ አቅራቢያ የሚገኘውና አገሬው የእኩልነት ተምሳሌት ነው የሚለው የሄልሲንኪ ግዙፉ ማዕከላዊ ቤተ-መጽሐፍት ኦዲ ይባላል። በውስጡ በርካታ አገልግሎቶችን ይዟል። ንባብ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ የባህልና ፈጠራ ታለንቶችን ያስተናግዳል። ከልጅ እስከ አዋቂ ለሁሉም ቦታ አለው። ፊንላንድ ዜጎቿ በደስታ ግብር የሚከፍሉባት አገር መሆኗን የአገሪቱ የታክስ አስተዳደር ሲናገር በኩራት ነው። ግብር መሰወር፤ ክፈሉ ብሎ በየግዜው መቀስቀስን የመሳሰሉ ነገሮች እዛ ቦታ የላቸውም። የኩባንያም ሆነ የግለሰብ ግብር ከፋዮች በታማኝነት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በወቅቱ እንደሚወጡ አስተዳደሩ ይገልጻል። ይህም የዜጎች ፍላጎትን ለማሟላት በተሰራ ስራ የተፈጠረ መሆኑን የተመለከትኳቸው ተቋማት ሃላፊዎች ይገልጻሉ። ዜጎች በመንግስት ላይ ከፍተኛ እምነት አላቸው። በፊንላንድ የዜጎች ደስተኝነት የሰላምና ነጻነት መገለጫ እንደሆነ ምሁራኖቻቸው በጥናት ስራዎቻቸው ጭምር ይመሰክራሉ። የደስታቸው ምንጭ ነጻና ጥራት ያለው ትምሕርት፣ በአካባቢ ጥበቃ፤ በፍትህና እኩልነት፤ በበጎ አድራጎት ተግባር፤ የእናቶችና ህጻናት ጤናን ጨምሮ አርአያ የሚሆኑ ጠንካራ የማሕበራዊ ደህንነትና ትስስር ስራዎች የመጡ ውጤቶች እንደሆኑ ይገለጻሉ። በጾታ እኩልነት ሴቶች በሁሉም መስክ ጥሩ ስፍራ አላቸው። በፖለቲካውም ከወንዶች ተቀራራቢ ቦታ እንዳላቸው የአገሪቱን ፓርላማ ስንጎበኝ ተረድቻለሁ። ከ200 የምክር ቤት አባላት 91ዱ ሴቶች ናቸው። የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ፊንላንድ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደስተኛ አገራት ደረጃ ላይ ለስምንት ተከታታይ ዓመታት የከፍታ ስፍራዋን ሳትለቅ በቁጥር አንድ ላይ እንድትቆይ አድርጓታል። ዜጎቿ በቀጣዩ ዓመትም ለዘጠነኛ ጊዜ የዓለም የደስተኞች አገር ሆና ትቀጥላለች የሚል እምነት አላቸው።