ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የምክክር ረቂቅ አጀንዳን ለባለድርሻ አካላት ማቅረብ እና ማስተቸት ለምን አስፈለገ?
May 25, 2026 48
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት ከሚኖሩ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አጀንዳ ሲያሰባስብ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ ኮሚሽኑ በዚህ ሂደት በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ባልተግባቡባቸው እጅግ መሠረታዊ የሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የምክክር አጀንዳዎቻቸውን እንዲሰጡ መደላድል ፈጥሯል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ኮሚሽኑ የተሰበሰበውን አጀንዳ አጠናክሮ እና ቀርፆ በማጠናቀቅ በምክክር ሀገራዊ መግባባት ሊደረግባቸው ያሻል ያላቸውን አዘጋጅቷል፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ኮሚሽኑ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔው ይመጥናሉ ብሎ የቀረፀውን ረቂቅ አጀንዳ ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት በማቅረብ ግብዓት በማሰባሰብ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ሂደት ለሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ብሎም ለአጀንዳ ቀረፃ የተለያዩ አበርክቶዎች እንደሚኖሩት የሚታመን ሲሆን የሚከተሉት ሃሳቦች ይህንን ያብራራሉ፡፡ 👉የአጀንዳ ሃሳቦች ትክክልኝነትን ከማረጋገጥ አንፃር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በርካታ ጉዳዮች በአጀንዳነት እንዲያዝላቸው ማቅረባቸውን ተከትሎ ያቀረቧቸው ሃሳቦች በምን ደረጃ ላይ እንዳሉ ለማወቅ ጉጉት ማሳደራቸው አጠያያቂ አይሆንም፡፡ በመሆኑም መሰል ተግባራት እና መድረኮች ኮሚሽኑ የባለድርሻ አካላትን አጀንዳ በአደራ ተረክቦ ሲቀርፅ በተፈለገው ቅርፅ ለታለመው ዓላማ መዘጋጀታቸውን ከእነዚሁ ባለድርሻ አካላት ጋር ማረጋገጡ ለምክክሩ ሂደት ጉልህ ሚናን ይጫወታል፡፡ 👉የሂደቱን ባለቤትነት ከማዳበር አንፃር የሀገራዊ ምክክር ረቂቅ አጀንዳን ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት አቅርቦ ማስተቸት እና በሂደቱ የእነዚህን አካላት ይሁንታ ለማግኘት መሻት ባለድርሻ አካላት በሂደቱ ላይ ያላቸውን የባለቤትነት መንፈስ ያጠናክርላቸዋል፡፡ ይህም ሁሉም አካላት በሂደቱ የሚኖራቸውን ሚና እንዲያጎለብቱ ያስችላቸዋል፡፡ 👉ግልፅነትን ከማጠናከር አንፃር ባለድርሻ አካላት በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሚመካከሩባቸውን የአጀንዳ ሃሳቦች ቀድመው ማወቃቸው እና ስለትክክለኛነታቸውም ይሁንታን መስጠታቸው ሂደቱን ግልፅ እና ተዓማኒ እንዲሆን ያግዘዋል፡፡ ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከመቀሌ 70 እንደርታ ለኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ለማለፍ ይጫወታሉ
May 25, 2026 78
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዋንጫ የመጀመሪያ የግማሽ ፍፃሜ መርሐ ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከመቀሌ 70 እንደርታ ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ጨዋታው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በሩብ ፍጻሜው መቻልን በመለያ ምት በማሸነፍ አራት ውስጥ ገብቷል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በበኩሉ በሩብ ፍጻሜው ቦዲቲ ከተማን 3 ለ 2 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። ሁለቱ ቡድኖች በዘንድሮው የውድድር ዓመት ለሶስተኛ ጊዜ ይገናኛሉ። በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሊጉ ሁለት ጊዜ ተገናኝተው በተመሳሳይ አንድ አንድ ጊዜ አሸንፈዋል። ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተገናኝተው መቀሌ 70 እንደርታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ፍፁም አለሙ እና ኮትዲቯራዊው አብዱላጢፍ ባምባ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ዳዊት ገብሩ ለወልዋሎ ግቧን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በፕሪሚየር ሊጉ በ40 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በ34 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። የጨዋታው አሸናፊ ቡድን በፍጻሜው ከሲዳማ ቡና እና ኢትዮጵያ መድን አሸናፊ ጋር ይጫወታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአፍሪካ ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
May 25, 2026 148
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመላው አፍሪካውያን ወንድሞችና እህቶች ለአፍሪካ ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ከ63 ዓመታት በፊት የአፍሪካ አባቶች እዚሁ አዲስ አበባ ላይ በመሰብሰብ ነፃ እና የተባበረች አህጉርን የመገንባት ታላቅ ህልም ማለማቸውን አስታውሰዋል። ይህ የአባቶች የአንድነት ህልም ዛሬም ድረስ ሳይደበዝዝ በደማቅ ሁኔታ መቀጠሉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ታሪካዊ ማዕከል መሆኗን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም በዚያው በታሪካዊው የአንድነት መንፈስ ከእያንዳንዱ የአፍሪካ አገር ጋር በጋራ ለመቆም ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ይሁን እንጂ አህጉሪቱን ለማበልጸግ የሚከናወኑ ተግባራት ገና ብዙ መሆናቸውን ጠቁመው፤ አሁን ካሉበት ደረጃ ይበልጥ ለመሻገር ከቃላት ወደ ተግባር፣ከቃል ኪዳንም ወደ ተጨባጭ ዕድገት መሸጋገር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። የአፍሪካ ታላቁ እና ዋነኛው ሀብት ምንጊዜም ቢሆን ሕዝቦቿ መሆናቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አህጉሪቱ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአንድነት የላቀ ከፍታ ላይ እንደርሳለን ሲሉ ገልጸዋል።
የአፍሪካ ቀን
May 25, 2026 109
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 ኢዜአ)፦ 63ኛው የአፍሪካ ቀን “የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስር እና ልማት፣ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ ይከበራል። የአፍሪካ አገራትና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ አፍሪካዊ ዳያስፖራዎችም ቀኑን በተለያዩ ሁነቶች ያከብሩታል። በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ቀኑ ዛሬ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል። ህብረቱ ባወጣው መግለጫ የዘንድሮው የአፍሪካ ቀን የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት) የተመሰረተበት 63ኛ ዓመት ታስቦ እንደሚውል አመልክቷል። የአፍሪካ ቀን ባለፉት ሁለት ቀናት በስፖርታዊ ውድድሮች፣አውደ ርዕዮች፣ባዛር፣ የመዝናኛ ጨዋታዎች እና በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር ቆይቷል። የቀኑ አከባባር ማጠቃለያ ስነ ስርዓት ዛሬ በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአባል ሀገራት ተወካዮች፣የአፍሪካ ዳያስፖራዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የልማት አጋሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ቀኑ በታሪክና በባህል ሀብታም በሆነችው አፍሪካ የአህጉሪቱ ሕዝቦች እርስ በእርስ የባህል፣ የኪነ ጥበብና ሌሎች ልምዳቸውን የሚያስተዋውቁበት መድረክም ነው። የአፍሪካ ቀን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማህበር ጋር በመሆን ከአባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶች እና ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች (RECs) ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁን የአፍሪካ ህብረት) እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን ተከትሎ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መጠሪያ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጠጣር በ2002 በደቡብ አፍሪካ ደርባን በተደረገ ጉባዔ ወደ አፍሪካ ህብረት መቀየሩ ይታወሳል። ቀኑ በየዓመቱ እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር ግንቦት 25 ይከበራል። በዓሉ የአፍሪካ ቀን ከመባሉ በፊት የአፍሪካ የነጻነት ቀን እየተባለ ይከበር ነበር።
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ቀን ውሎ
May 24, 2026 477
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ማምሻውን ተጠናቋል። ሁሉም የ38ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሰዓት ተደርገዋል:: የሻምፒዮኖቹ አርሰናል የድል ፌሽታ ሲያነሳ፣ የጎረቤቱ ቶተንሃም ከመውረድ መትረፍ፣ የዌስትሃም ከሊጉ መሰናበት፣ የሊቨርፑል የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ማረጋገጥ እና የብሩኖ ፈርናንዴዝ አዲስ ክብረ ወሰን፤ እለቱን በክስተቶች የታጀበ አድርጎታል። በሳምንቱ አጋማሽ ከ22 ዓመታት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋገጠው አርሰናል ለረጅም ጊዜ የናፈቀውን ዋንጫ በደማቅ ስነ ስርዓት አንስቷል። መድፈኞቹ በሰልኸረስት ፓርክ ባደረጉት ጨዋታ ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 አሸንፈዋል። ጋብርኤል ጄሱስ እና ኖኒ ማዱዌኬ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጂን ፍሊፕ ማቴታ የፓላስን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። አርሰናል በ85 ነጥብ ዓመቱን በአንደኝነት ተጠናቋል። ከጨዋታው በፊት የክሪስታል ፓላስ ተጫዋቾች በግራ እና በቀኝ በመቆም ለሻምፒዮኑ አርሰናል የክብር አቀባበል (Guard of honour) አድርገዋል። ተከታዩ ማንችስተር ሲቲ በአስቶንቪላ የ2 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል። ኦሊ ዋትኪንስ ለቪላ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥሯል። አንቶዋን ሴሜኒዮ የሲቲን ጎል ከመረብ አገናኝቷል። ሲቲ በ78 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። የውሃ ሰማያዊዎቹ አሰልጣኝ ፔፔ ጋርዲዮላ ከጨዋታው በኋላ ክለቡን በይፋ ተሰናብቷል። በርናንዶ ሲልቫም ሲቲን ተሰናብቷል። የማንችስተር ሲቲው አርሊንግ ሃላንድ በ27 ጎሎች የሊጉ ኮከብ ግብ አስቆጣሪ በመሆን ተጠናቋል። በሊጉ የመዝጊያ ቀን ሲጠበቁ ከነበሩ ጉዳዮች መካከል አንዱ ላለመውረድ የሚደረግ ትግል ነው። ቶተንሃም ሆትስፐርስ በሜዳው ኤቨርተንን አስተናግዶ 1 ለ 0 በማሸነፍ በ41 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል። ጆአኦ ፓሊኒያ የስፐርስን ብቸኛ ጎል አስቆጥሯል። ዌስትሃም ዩናይትድ ሊድስ ዩናይትድን 3 ለ 0 ቢያሸንፍም ከሊጉ ወርዷል። ቫለንቲን ካስቴላኖስ፣ጃሬድ ቦወን እና ካሉም ዊልሰን ግቦቹን አስቆጥረዋል። ዌስትሃም ዩናይትድ በ39 ነጥብ 18ኛ ደረጃን በመያዝ ከሊጉ ተሰናብቷል። የለንደኑ ክለብ ከ14 ዓመታት የሊጉ ቆይታ በኋላ ወደ ሻምፒዮንሺፑ ወርዷል። ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ አንድ አቻ በመለያየት በ60 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን አረጋግጧል። መሐመድ ሳላህ እና አንዲ ሮበርትሰን ከጨዋታው በኋላ ሊቨርፑልን በይፋ ተሰናብተዋል። ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በመርታት በ54 ነጥብ የዩሮፓ ሊግ ተሳታፊነት ትኬቱን ቆርጧል። ቦርንማውዝ ሌላኛው የዩሮፓ ተሳታፊ ክለብ ነው። ቡዱኑ ዛሬ ከኖቲንግሃም ፎረስት ጋር አንድ አቻ በመለያየት በ57 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። ቼልሲ በ52 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዞ በመጨረስ ከአውሮፓ መድረክ ተሳትፎ ውጪ ሆኗል። ማንችስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 አሸንፏል። በአሜክስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፓትሪክ ዶርጉ፣ ብሪያን ምቡዌሞ እና ብሩኖ ፈርናንዴዝ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ለዶርጉ ጎል መቆጠር እጁ የነበረበት ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዓመቱ 21 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል። ከዚህ ቀደም ቲዬሪ ሄነሪ እና ኬቨን ደ ብሮይን (በተመሳሳይ 20 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል) በጣምራ ይዘው የነበሩትን ክብረ ወሰን አሻሽሏል። ፈርናንዴዝ ትናንት የሊጉ የዓመቱ ምርጣ ተጫዋች በመባል መመረጡ አይዘነጋም። ዩናይትድ በ71 ነጥብ ሶስተኛ ሆኖ ዓመቱን አጠናቋል። ብራይተን በ53 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በኮንፍረንስ ሊግ መሳተፉን አረጋግጧል። ፋልሃም ኒውካስትል ዩናይትድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ወራጆቹ በርንሌይ እና ዎልቭስ ባደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይተዋል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እስከ መጨረሻው ደቂቃ በድራማ እና ትዕይንቶች ታጅቦ ተጠናቋል።
ፖለቲካ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአፍሪካ ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
May 25, 2026 148
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመላው አፍሪካውያን ወንድሞችና እህቶች ለአፍሪካ ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ከ63 ዓመታት በፊት የአፍሪካ አባቶች እዚሁ አዲስ አበባ ላይ በመሰብሰብ ነፃ እና የተባበረች አህጉርን የመገንባት ታላቅ ህልም ማለማቸውን አስታውሰዋል። ይህ የአባቶች የአንድነት ህልም ዛሬም ድረስ ሳይደበዝዝ በደማቅ ሁኔታ መቀጠሉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ታሪካዊ ማዕከል መሆኗን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም በዚያው በታሪካዊው የአንድነት መንፈስ ከእያንዳንዱ የአፍሪካ አገር ጋር በጋራ ለመቆም ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ይሁን እንጂ አህጉሪቱን ለማበልጸግ የሚከናወኑ ተግባራት ገና ብዙ መሆናቸውን ጠቁመው፤ አሁን ካሉበት ደረጃ ይበልጥ ለመሻገር ከቃላት ወደ ተግባር፣ከቃል ኪዳንም ወደ ተጨባጭ ዕድገት መሸጋገር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። የአፍሪካ ታላቁ እና ዋነኛው ሀብት ምንጊዜም ቢሆን ሕዝቦቿ መሆናቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አህጉሪቱ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአንድነት የላቀ ከፍታ ላይ እንደርሳለን ሲሉ ገልጸዋል።
የአፍሪካ ቀን
May 25, 2026 109
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 ኢዜአ)፦ 63ኛው የአፍሪካ ቀን “የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስር እና ልማት፣ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ ይከበራል። የአፍሪካ አገራትና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ አፍሪካዊ ዳያስፖራዎችም ቀኑን በተለያዩ ሁነቶች ያከብሩታል። በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ቀኑ ዛሬ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል። ህብረቱ ባወጣው መግለጫ የዘንድሮው የአፍሪካ ቀን የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት) የተመሰረተበት 63ኛ ዓመት ታስቦ እንደሚውል አመልክቷል። የአፍሪካ ቀን ባለፉት ሁለት ቀናት በስፖርታዊ ውድድሮች፣አውደ ርዕዮች፣ባዛር፣ የመዝናኛ ጨዋታዎች እና በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር ቆይቷል። የቀኑ አከባባር ማጠቃለያ ስነ ስርዓት ዛሬ በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአባል ሀገራት ተወካዮች፣የአፍሪካ ዳያስፖራዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የልማት አጋሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ቀኑ በታሪክና በባህል ሀብታም በሆነችው አፍሪካ የአህጉሪቱ ሕዝቦች እርስ በእርስ የባህል፣ የኪነ ጥበብና ሌሎች ልምዳቸውን የሚያስተዋውቁበት መድረክም ነው። የአፍሪካ ቀን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማህበር ጋር በመሆን ከአባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶች እና ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች (RECs) ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁን የአፍሪካ ህብረት) እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን ተከትሎ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መጠሪያ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጠጣር በ2002 በደቡብ አፍሪካ ደርባን በተደረገ ጉባዔ ወደ አፍሪካ ህብረት መቀየሩ ይታወሳል። ቀኑ በየዓመቱ እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር ግንቦት 25 ይከበራል። በዓሉ የአፍሪካ ቀን ከመባሉ በፊት የአፍሪካ የነጻነት ቀን እየተባለ ይከበር ነበር።
ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማህበረሰቡን የመልማትና የማደግ ጥያቄ በመመለስ ለውጥ ማምጣት ችሏል
May 24, 2026 626
ደብረ ማርቆስ፤ ግንቦት16/2018 (ኢዜአ)፡ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማህበረሰቡን የመልማት እና የማደግ ጥያቄዎችን በየደረጃው ምላሽ በመስጠት የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡ ተገለጸ። ብልጽግና ፓርቲ በምስራቅ ጎጃም ዞን አነደድ ወረዳ አንበር ከተማ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሄዷል። "በላቀ ህዝባዊ ተሳትፎ፣ ኢትዮጵያን ወደ ተምሣሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የምረጡኝ ቅስቀሳ የወረዳው አመራሮችን ጨምሮ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ በወቅቱ እንደገለፁት፤ ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎችን በማከናወን ውጤት ማስመዝገብ ችሏል። በተለይም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማህበረሰቡን የመልማት፣ የማደግ እና የለውጥ ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስ በተሰሩ ስራዎች እመርታዊ ለውጥ ማስመዝገብ መቻሉን ገልፀዋል። አሁንም የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ እቅዶች ታቅደው እየተተገበሩ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ ይኸንኑ የበለጠ አጠናክሮ ለማስቀጠልም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲውን በመምረጥ ልማትን ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል። ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የስልጡንነት መገለጫ መሆኑን ጠቅሰው፤ ምርጫው ሰላማዊ እና በህዝብ ዘንድ ታማኝነትን ያተረፈ ሆኖ እንዲከናወንም ህብረተሰቡ የአካባቢውን ሰላም በማረጋገጥ የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። የአነደድ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አየለ ድረስ በበኩላቸው፤ ምርጫ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል ነው ብለዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የማይቀለበስ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚረጋገጥበት እና ዜጎች የሚሆናቸውን ፓርቲ ለመምረጥ ነጻነት የሚጎናጸፉበት አንደሚሆንም ገልፀዋል። መንግስት ከዚህ በፊት ለህዝብ ቃል የገባቸውን የልማት አጀንዳዎች በየደረጃው እየመለሰ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ለወደፊትም የለማች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ፓርቲው የቤት ስራ ይወስዳል ብለዋል። በድጋፍ ሰልፉ የተሳተፉት ወይዘሮ አልማው ወንዴ እንዳሉት፤ እንደ ሀገር ልማት፣ እድገት እና ሰላም ስለምንፈልግ ይህን ሊያስቀጥል የሚችለውን ፓርቲ እንመርጣለን ብለዋል። ከምንም በላይ ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። አቶ ዳንኤል ታደሰ በበኩላቸው ምርጫ ሀገርን ለማስቀጠል የሚደረግ ሂደት መሆኑን ገልጸዋል። እሳቸውም ሰላማዊ ምርጫ ተካሄዶ ሀገር እንድትቀጥል ለህዝብ የልማት ተጠቃሚነትና ሰላም መረጋገጥ የሚሰራውን ፓርቲ በመለየት ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
የዳውሮ እና የኮንታ ዞን ነዋሪዎች በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ለዴሞክራዊያዊ ሥርአት ግንባታ የበኩላቸውን ለመወጣት ተዘጋጅተዋል
May 24, 2026 420
ቦንጋ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ይበጀኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ በመምረጥ ለዴሞክራሲያዊ ሥርአት ግንባታ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዳውሮ እና የኮንታ ዞን ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የዳውሮ እና የኮንታ ዞን ነዋሪዎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ወስደው የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ትዕግስት አየለ፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገር እድገት የተሻለ አማራጭ ሀሳብ ይዞ የቀረበን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ በመገናኛ ብዙሃን ሲቀርቡ የነበሩ ክርክሮችን በትኩረት መከታተላቸውን አንስተዋል። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርአት ግንባታ መሰረት በመሆኑ የዜጎችን የነቃ ተሳትፎ ይጠይቃል ያሉት ወይዘሮ ትዕግስት ለዚህም በድምጻቸው መሪያቸውን ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ሌላኛው በዞኑ የቶጫ ወረዳ ነዋሪ አቶ ታምራት ይፍሩ በበኩላቸው፣ ይበጀኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ በምርጫ ካርዳቸው ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል። ከዚህ ባለፈ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ እንዲሆን የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች በወሰዱት ካርድ ድምጻቸውን ለሚፈልጉት ፓርቲ በነጻነት በመስጠት ሀገርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩላቸውን እንዲወጡም መክረዋል፡፡ በኮንታ ዞን የኮንታ ኮይሻ ወረዳ ነዋሪ አቶ አድነው አባተ፣ በወሰዱት ካርድ የሀገርን ብልጽግናና ብሔራዊ ጥቅም ያስጠብቃል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መወሰናቸውን ገልፀዋል። ምርጫ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፣ በሂደቱም አንድ ድምጽ ዋጋ እንዳለው ዜጎች መረዳትእንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ ሌላኛው የወረዳው ነዋሪ አቶ አረጋ አስፋው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚስችላቸውን ካርድ ይዘው የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ ነው፡፡ ምርጫ በአምስት ዓመት አንዴ የሚመጣ ትልቅ ሀገራዊ ኩነት በመሆኑ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጡት ገልጸው፣ በምርጫውም በእውቀት ላይ የተመሰረተ ድምፅ ለመስጠት በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ለእዚህም በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን የተላለፉትን የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውን አመልክተዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተዓማኒና ፍትኃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በጋራ እየሰራን ነው-የፖለቲካ ፓርቲዎች
May 24, 2026 560
ጋምቤላ ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፡- 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተዓማኒና ፍትኃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን በጋምቤላ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ገለፁ። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ለማጠናቀቅ የምዝገባ፣ የዕጩዎች ጥቆማ እና የሎጂስቲክስ ዝግጅቶችን እያጠናቀቀ ይገኛል። በተለይም ምርጫው ሰላማዊ እና ተዓማኒ እንዲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑ የሚገለጽ ሲሆን፣ ፓርቲዎቹም የምርጫ ስነ-ምግባር ደንብን በማክበርና ደጋፊዎቻቸውን በማንቃት ረገድ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ በተደጋጋሚ ጥሪ ሲቀርብ መቆየቱ ይታወሳል። በጋምቤላ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለኢዜአ እንደገለፁት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ፍትኃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በጋራ እየሰሩ ነው። ከተፎካካሪ ፓርቲዎቹ መካከል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ተወካይ አቶ ኡፓዲ አኳይ እንዳሉት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም እንከን እንዲከናወን ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በቅንጅት እየሰሩ ናቸው። በተለይም ዜጎች ያመኑበትን ፓርቲ በነፃነት መምረጥ እንዲችሉ በፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በኩል ሰፊ ስራዎች ማከናወናቸውን ገልፀዋል። ፓርቲው ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፕሮግራሞቹንና ፖሊሲዎቹን ለመራጩ ህዝብ ያለምንም ችግር ማቅረቡን ጠቅሰዋል። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት ካለፉት የምርጫ ጊዜያት በተሻለ መልኩ የፖለቲካ ምህዳሩን ያሰፋ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ተወካይ አቶ ሬክ ኖክ ናቸው። የፓርቲዎችን ማኒፌስቶ መራጩ ህዝብ በቀላሉ በሚሰማውና በሚረዳው ቋንቋ እንዲቀርብ መደረጉን ለአብነት በማንሳት። የህዳሴ ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ተወካይ መምህር ሻምበል ቶላ በበኩላቸው በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው መንግስት ለመመስረት ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የላቀ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ህዳሴ ፓርቲ በነፃነት ፕሮግራሞቹንና ፖሊሲዎቹን በተለያዩ ሚዲያዎችና መድረኮች ማስተዋወቁን ገልፀው ሂደቱም ፍፁም ሰላማዊ እንደነበር አንስተዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ ህዳሴ ፓርቲ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ተባብሮ እንደሚሰራም ገልፀዋል። መራጩ ህዝብም በወሰደው ካርድ ሀገርንና ህዝብን የሚጠቅም ሀሳብ ያለውን ፓርቲ በመምረጥ ህገ-መንግስታዊ መብቱን ሊጠቀም እንደሚገባ የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮቹ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጠንካራ የተቋም ግንባታና ብቁ የፖሊስ ሃይል የማፍራት ስራ በውጤታማነት እንደቀጠለ ነው - ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል
May 24, 2026 536
ድሬደዋ ፣ ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጠንካራ የተቋም ግንባታና ብቁ የፖሊስ ሃይል የማፍራት ስራ በውጤታማነት እንደቀጠለ የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በድሬደዋ ያስገነባውን የምስራቅ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ዘመናዊ ማዕከል አስመርቆ አገልግሎት አስጀምሯል። ማዕከሉን መርቀው በይፋ ስራ ያስጀመሩት የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፤ ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በዘመናዊና ጠንካራ አደረጃጀት በመታገዝ ሀገራዊ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት ለመወጣት የሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል። በድሬዳዋ የተገነባው ዘመናዊ የፈጥኖ ደራሽ ማዕከልም የዚሁ ጥረት ማሳያ መሆኑን አንስተው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጠንካራ የተቋም ግንባታና ብቁ የፖሊስ ሃይል የማፍራት ስራ በውጤታማነት እንደቀጠለ ገልጸዋል። የማዕከሉ ስራ መጀመር በኢትዮጵያ ዋነኛ የገቢና ወጪ እንቅስቃሴ እንዲሁም ቀጣናውን በአስተማማኝ መልኩ ለማስጠበቅ የተደመረ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። በማዕከሉ የወንጀል ምርመራ ኃይልን በማደራጀት ወንጀልን በላቀ እና በተሻለ ደረጃ ለመከላከልም ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዘመናዊ የተቋማት ግንባታና የሰው ሃይል ልማትን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ በድሬዳዋ የተገነባው ዘመናዊ የፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ማዕከሉ ለምስራቅ ተጎራባች ክልሎች አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን ትልቅ አቅም መሆኑን አንስተዋል። የወጪና የገቢ ንግድ እንቅስቃሴዎችን በአስተማማኝ መንገድ ለማካሄድና ለቀጣናው ሰላም ወሳኝ ነው ብለዋል። በመሆኑም በማዕከሉ ለሚከናወኑ ስራዎች አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ ለማዕከሉ መገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና ድርጅቶች ሽልማትና ዕውቅና ተሰጥቷል።
ብልፅግና ፓርቲ የሕዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎችን አከናውኗል
May 24, 2026 600
አዲስ አበባ፤ግንቦት 16 /2018 (ኢዜአ)፦ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራትን በማከናወን ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሃማን ገለፁ። የብልፅግና ፓርቲ “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የምረጡኝ ቅስቀሳ መርሃግብር በሸገር ከተማ በርካታ ቁጥር ያላቸው የፓርቲው ደጋፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል። ከማለዳው ጀምሮ የከተማዋ ነዋሪዎችና የፓርቲው ደጋፊዎች በለገጣፎ ስታዲየም በመገኘት ለፓርቲው ያላቸውን ድጋፍና አጋርነት ገልፀዋል። በመርሃግብሩ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሃማን፣ የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) እና ሌሎች የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሃማን ብልፅግና ፓርቲ የጀመረውን ሀገር የመገንባትና የልማት ጉዞ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚህም ጥራትንና ፍጥነትን መመሪያ በማድረግ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በርካታ ፕሮጀክቶች ተቀርጸው ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ሥራዎች መሰራቱን ጠቅሰዋል። ፓርቲው የገባውን ቃልና የጀመራቸውን የልማት ሥራዎች ዳር ለማድረስ በቁርጠኝነት እየሰራ ውጤቱ በተጨባጭ እየታየ እንዳለ ተናግረዋል። በክልሉ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራትን ማከናወኑን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት ሦስት ዓመታት በሸገር ከተማ ዘመናዊ ከተማ የመገንባት ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም የመንገድ መሰረተ ልማቶ፣ የሆስፒታሎችና የትምህርት ቤቶች ግንባታን በማካሄድ ከፍተኛ የማኅበራዊ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል። እንዲሁም እንደሀገር የተቀረፁ የግብርና እና የኢኮኖሚ ዕቅዶችን በከተማ ደረጃ ስኬታማ ሥራ ለመስራት ማስቻሉን ተናግረዋል። ይህ ተግባርም ብልፅግና የሐሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባር የሚታዩ ሰፋፊ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ተናግረዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ጠቅላላ ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት ሊሳተፉ ይገባል
May 23, 2026 874
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች የነቃ ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት እናታለም እንዳለ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር "በፖለቲካ፣ በምርጫና ሰላም ግንባታ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ማጎልበት" በሚል መሪ ሃሳብ ከማህበሩ አባላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል። የማህበሩ ፕሬዚዳንት እናታለም እንዳለ በዚሁ ወቅት፤ ማህበሩ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና እኩል ተሳታፊነትን የማረጋገጥ ዓላማ ይዞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሴቶች የመምረጥና የመመረጥ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በመንግስት አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ የነቃ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚያግዙ የአቅም ግንባታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 2 ሺህ 200 የማህበሩ አባል የሆኑ ሴቶች ሰልጥነው የታዛቢነት ፍቃድ መውሰዳቸውንም ጠቁመዋል። በተጨማሪም ሌሎችም ዕድሜያቸው ለምርጫ የደረሱ የማህበረሰብ ክፍሎች በምርጫው በመሳተፍ የሚመራቸውን መንግስት በድምፃቸው መምረጥ እንዲችሉ የማስገንዘብ ስራ እያከናውኑ መሆኑን ገልጸዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም ሴቶች በሃገር ሰላምና ፖለቲካ ውስጥ ያላቸውን የላቀ ፋይዳ በመገንዘብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድርሻቸውን እንዲወጡ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል። ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል። የህብረተሰቡ ግንዛቤ ለማሳደግ ቤት ለቤት በመሄድና የተለያዩ መርሃግብሮችን በማዘጋጀት ለምርጫው አሳታፊነት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የገለጹት የማህበሩ አባል ወይዘሮ መሰረት ሶርሳ ናቸው። ወይዘሮ አዳነች አሉላ በበኩላቸው፤ ለምርጫ የደረሱ ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ በማስተማር የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ከ513 ሺህ በላይ አባላት እንዳለው ተመላክቷል።
ፖለቲካ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአፍሪካ ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
May 25, 2026 148
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመላው አፍሪካውያን ወንድሞችና እህቶች ለአፍሪካ ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ከ63 ዓመታት በፊት የአፍሪካ አባቶች እዚሁ አዲስ አበባ ላይ በመሰብሰብ ነፃ እና የተባበረች አህጉርን የመገንባት ታላቅ ህልም ማለማቸውን አስታውሰዋል። ይህ የአባቶች የአንድነት ህልም ዛሬም ድረስ ሳይደበዝዝ በደማቅ ሁኔታ መቀጠሉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ታሪካዊ ማዕከል መሆኗን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬም በዚያው በታሪካዊው የአንድነት መንፈስ ከእያንዳንዱ የአፍሪካ አገር ጋር በጋራ ለመቆም ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ይሁን እንጂ አህጉሪቱን ለማበልጸግ የሚከናወኑ ተግባራት ገና ብዙ መሆናቸውን ጠቁመው፤ አሁን ካሉበት ደረጃ ይበልጥ ለመሻገር ከቃላት ወደ ተግባር፣ከቃል ኪዳንም ወደ ተጨባጭ ዕድገት መሸጋገር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። የአፍሪካ ታላቁ እና ዋነኛው ሀብት ምንጊዜም ቢሆን ሕዝቦቿ መሆናቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አህጉሪቱ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአንድነት የላቀ ከፍታ ላይ እንደርሳለን ሲሉ ገልጸዋል።
የአፍሪካ ቀን
May 25, 2026 109
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 ኢዜአ)፦ 63ኛው የአፍሪካ ቀን “የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስር እና ልማት፣ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ ይከበራል። የአፍሪካ አገራትና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ አፍሪካዊ ዳያስፖራዎችም ቀኑን በተለያዩ ሁነቶች ያከብሩታል። በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ቀኑ ዛሬ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል። ህብረቱ ባወጣው መግለጫ የዘንድሮው የአፍሪካ ቀን የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት) የተመሰረተበት 63ኛ ዓመት ታስቦ እንደሚውል አመልክቷል። የአፍሪካ ቀን ባለፉት ሁለት ቀናት በስፖርታዊ ውድድሮች፣አውደ ርዕዮች፣ባዛር፣ የመዝናኛ ጨዋታዎች እና በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር ቆይቷል። የቀኑ አከባባር ማጠቃለያ ስነ ስርዓት ዛሬ በአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአባል ሀገራት ተወካዮች፣የአፍሪካ ዳያስፖራዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የልማት አጋሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ቀኑ በታሪክና በባህል ሀብታም በሆነችው አፍሪካ የአህጉሪቱ ሕዝቦች እርስ በእርስ የባህል፣ የኪነ ጥበብና ሌሎች ልምዳቸውን የሚያስተዋውቁበት መድረክም ነው። የአፍሪካ ቀን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማህበር ጋር በመሆን ከአባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶች እና ከቀጣናዊ ኢኮኖሚ ማህበረሰቦች (RECs) ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁን የአፍሪካ ህብረት) እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን ተከትሎ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መጠሪያ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጠጣር በ2002 በደቡብ አፍሪካ ደርባን በተደረገ ጉባዔ ወደ አፍሪካ ህብረት መቀየሩ ይታወሳል። ቀኑ በየዓመቱ እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር ግንቦት 25 ይከበራል። በዓሉ የአፍሪካ ቀን ከመባሉ በፊት የአፍሪካ የነጻነት ቀን እየተባለ ይከበር ነበር።
ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማህበረሰቡን የመልማትና የማደግ ጥያቄ በመመለስ ለውጥ ማምጣት ችሏል
May 24, 2026 626
ደብረ ማርቆስ፤ ግንቦት16/2018 (ኢዜአ)፡ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማህበረሰቡን የመልማት እና የማደግ ጥያቄዎችን በየደረጃው ምላሽ በመስጠት የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡ ተገለጸ። ብልጽግና ፓርቲ በምስራቅ ጎጃም ዞን አነደድ ወረዳ አንበር ከተማ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሄዷል። "በላቀ ህዝባዊ ተሳትፎ፣ ኢትዮጵያን ወደ ተምሣሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የምረጡኝ ቅስቀሳ የወረዳው አመራሮችን ጨምሮ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ በወቅቱ እንደገለፁት፤ ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎችን በማከናወን ውጤት ማስመዝገብ ችሏል። በተለይም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማህበረሰቡን የመልማት፣ የማደግ እና የለውጥ ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስ በተሰሩ ስራዎች እመርታዊ ለውጥ ማስመዝገብ መቻሉን ገልፀዋል። አሁንም የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ እቅዶች ታቅደው እየተተገበሩ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ ይኸንኑ የበለጠ አጠናክሮ ለማስቀጠልም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲውን በመምረጥ ልማትን ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል። ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የስልጡንነት መገለጫ መሆኑን ጠቅሰው፤ ምርጫው ሰላማዊ እና በህዝብ ዘንድ ታማኝነትን ያተረፈ ሆኖ እንዲከናወንም ህብረተሰቡ የአካባቢውን ሰላም በማረጋገጥ የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። የአነደድ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አየለ ድረስ በበኩላቸው፤ ምርጫ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል ነው ብለዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የማይቀለበስ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚረጋገጥበት እና ዜጎች የሚሆናቸውን ፓርቲ ለመምረጥ ነጻነት የሚጎናጸፉበት አንደሚሆንም ገልፀዋል። መንግስት ከዚህ በፊት ለህዝብ ቃል የገባቸውን የልማት አጀንዳዎች በየደረጃው እየመለሰ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ለወደፊትም የለማች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ፓርቲው የቤት ስራ ይወስዳል ብለዋል። በድጋፍ ሰልፉ የተሳተፉት ወይዘሮ አልማው ወንዴ እንዳሉት፤ እንደ ሀገር ልማት፣ እድገት እና ሰላም ስለምንፈልግ ይህን ሊያስቀጥል የሚችለውን ፓርቲ እንመርጣለን ብለዋል። ከምንም በላይ ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። አቶ ዳንኤል ታደሰ በበኩላቸው ምርጫ ሀገርን ለማስቀጠል የሚደረግ ሂደት መሆኑን ገልጸዋል። እሳቸውም ሰላማዊ ምርጫ ተካሄዶ ሀገር እንድትቀጥል ለህዝብ የልማት ተጠቃሚነትና ሰላም መረጋገጥ የሚሰራውን ፓርቲ በመለየት ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
የዳውሮ እና የኮንታ ዞን ነዋሪዎች በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ለዴሞክራዊያዊ ሥርአት ግንባታ የበኩላቸውን ለመወጣት ተዘጋጅተዋል
May 24, 2026 420
ቦንጋ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ይበጀኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ በመምረጥ ለዴሞክራሲያዊ ሥርአት ግንባታ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዳውሮ እና የኮንታ ዞን ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የዳውሮ እና የኮንታ ዞን ነዋሪዎች ለመራጭነት የሚያበቃቸውን ካርድ ወስደው የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ትዕግስት አየለ፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገር እድገት የተሻለ አማራጭ ሀሳብ ይዞ የቀረበን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ በመገናኛ ብዙሃን ሲቀርቡ የነበሩ ክርክሮችን በትኩረት መከታተላቸውን አንስተዋል። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርአት ግንባታ መሰረት በመሆኑ የዜጎችን የነቃ ተሳትፎ ይጠይቃል ያሉት ወይዘሮ ትዕግስት ለዚህም በድምጻቸው መሪያቸውን ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ሌላኛው በዞኑ የቶጫ ወረዳ ነዋሪ አቶ ታምራት ይፍሩ በበኩላቸው፣ ይበጀኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ በምርጫ ካርዳቸው ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል። ከዚህ ባለፈ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ እንዲሆን የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች በወሰዱት ካርድ ድምጻቸውን ለሚፈልጉት ፓርቲ በነጻነት በመስጠት ሀገርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩላቸውን እንዲወጡም መክረዋል፡፡ በኮንታ ዞን የኮንታ ኮይሻ ወረዳ ነዋሪ አቶ አድነው አባተ፣ በወሰዱት ካርድ የሀገርን ብልጽግናና ብሔራዊ ጥቅም ያስጠብቃል ያሉትን ፓርቲ ለመምረጥ መወሰናቸውን ገልፀዋል። ምርጫ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፣ በሂደቱም አንድ ድምጽ ዋጋ እንዳለው ዜጎች መረዳትእንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ ሌላኛው የወረዳው ነዋሪ አቶ አረጋ አስፋው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም የሚስችላቸውን ካርድ ይዘው የድምጽ መስጫውን ቀን እየተጠባበቁ ነው፡፡ ምርጫ በአምስት ዓመት አንዴ የሚመጣ ትልቅ ሀገራዊ ኩነት በመሆኑ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጡት ገልጸው፣ በምርጫውም በእውቀት ላይ የተመሰረተ ድምፅ ለመስጠት በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ለእዚህም በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን የተላለፉትን የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውን አመልክተዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተዓማኒና ፍትኃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በጋራ እየሰራን ነው-የፖለቲካ ፓርቲዎች
May 24, 2026 560
ጋምቤላ ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፡- 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተዓማኒና ፍትኃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን በጋምቤላ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ገለፁ። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ለማጠናቀቅ የምዝገባ፣ የዕጩዎች ጥቆማ እና የሎጂስቲክስ ዝግጅቶችን እያጠናቀቀ ይገኛል። በተለይም ምርጫው ሰላማዊ እና ተዓማኒ እንዲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑ የሚገለጽ ሲሆን፣ ፓርቲዎቹም የምርጫ ስነ-ምግባር ደንብን በማክበርና ደጋፊዎቻቸውን በማንቃት ረገድ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ በተደጋጋሚ ጥሪ ሲቀርብ መቆየቱ ይታወሳል። በጋምቤላ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለኢዜአ እንደገለፁት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ፍትኃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በጋራ እየሰሩ ነው። ከተፎካካሪ ፓርቲዎቹ መካከል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ተወካይ አቶ ኡፓዲ አኳይ እንዳሉት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም እንከን እንዲከናወን ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በቅንጅት እየሰሩ ናቸው። በተለይም ዜጎች ያመኑበትን ፓርቲ በነፃነት መምረጥ እንዲችሉ በፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በኩል ሰፊ ስራዎች ማከናወናቸውን ገልፀዋል። ፓርቲው ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፕሮግራሞቹንና ፖሊሲዎቹን ለመራጩ ህዝብ ያለምንም ችግር ማቅረቡን ጠቅሰዋል። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት ካለፉት የምርጫ ጊዜያት በተሻለ መልኩ የፖለቲካ ምህዳሩን ያሰፋ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ተወካይ አቶ ሬክ ኖክ ናቸው። የፓርቲዎችን ማኒፌስቶ መራጩ ህዝብ በቀላሉ በሚሰማውና በሚረዳው ቋንቋ እንዲቀርብ መደረጉን ለአብነት በማንሳት። የህዳሴ ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ተወካይ መምህር ሻምበል ቶላ በበኩላቸው በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው መንግስት ለመመስረት ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የላቀ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ህዳሴ ፓርቲ በነፃነት ፕሮግራሞቹንና ፖሊሲዎቹን በተለያዩ ሚዲያዎችና መድረኮች ማስተዋወቁን ገልፀው ሂደቱም ፍፁም ሰላማዊ እንደነበር አንስተዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ ህዳሴ ፓርቲ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ተባብሮ እንደሚሰራም ገልፀዋል። መራጩ ህዝብም በወሰደው ካርድ ሀገርንና ህዝብን የሚጠቅም ሀሳብ ያለውን ፓርቲ በመምረጥ ህገ-መንግስታዊ መብቱን ሊጠቀም እንደሚገባ የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮቹ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጠንካራ የተቋም ግንባታና ብቁ የፖሊስ ሃይል የማፍራት ስራ በውጤታማነት እንደቀጠለ ነው - ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል
May 24, 2026 536
ድሬደዋ ፣ ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጠንካራ የተቋም ግንባታና ብቁ የፖሊስ ሃይል የማፍራት ስራ በውጤታማነት እንደቀጠለ የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በድሬደዋ ያስገነባውን የምስራቅ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ዘመናዊ ማዕከል አስመርቆ አገልግሎት አስጀምሯል። ማዕከሉን መርቀው በይፋ ስራ ያስጀመሩት የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፤ ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በዘመናዊና ጠንካራ አደረጃጀት በመታገዝ ሀገራዊ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት ለመወጣት የሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል። በድሬዳዋ የተገነባው ዘመናዊ የፈጥኖ ደራሽ ማዕከልም የዚሁ ጥረት ማሳያ መሆኑን አንስተው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጠንካራ የተቋም ግንባታና ብቁ የፖሊስ ሃይል የማፍራት ስራ በውጤታማነት እንደቀጠለ ገልጸዋል። የማዕከሉ ስራ መጀመር በኢትዮጵያ ዋነኛ የገቢና ወጪ እንቅስቃሴ እንዲሁም ቀጣናውን በአስተማማኝ መልኩ ለማስጠበቅ የተደመረ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። በማዕከሉ የወንጀል ምርመራ ኃይልን በማደራጀት ወንጀልን በላቀ እና በተሻለ ደረጃ ለመከላከልም ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። በቀጣይም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዘመናዊ የተቋማት ግንባታና የሰው ሃይል ልማትን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ በድሬዳዋ የተገነባው ዘመናዊ የፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ማዕከሉ ለምስራቅ ተጎራባች ክልሎች አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን ትልቅ አቅም መሆኑን አንስተዋል። የወጪና የገቢ ንግድ እንቅስቃሴዎችን በአስተማማኝ መንገድ ለማካሄድና ለቀጣናው ሰላም ወሳኝ ነው ብለዋል። በመሆኑም በማዕከሉ ለሚከናወኑ ስራዎች አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ ለማዕከሉ መገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና ድርጅቶች ሽልማትና ዕውቅና ተሰጥቷል።
ብልፅግና ፓርቲ የሕዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎችን አከናውኗል
May 24, 2026 600
አዲስ አበባ፤ግንቦት 16 /2018 (ኢዜአ)፦ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራትን በማከናወን ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሃማን ገለፁ። የብልፅግና ፓርቲ “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የምረጡኝ ቅስቀሳ መርሃግብር በሸገር ከተማ በርካታ ቁጥር ያላቸው የፓርቲው ደጋፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል። ከማለዳው ጀምሮ የከተማዋ ነዋሪዎችና የፓርቲው ደጋፊዎች በለገጣፎ ስታዲየም በመገኘት ለፓርቲው ያላቸውን ድጋፍና አጋርነት ገልፀዋል። በመርሃግብሩ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሃማን፣ የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) እና ሌሎች የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሃማን ብልፅግና ፓርቲ የጀመረውን ሀገር የመገንባትና የልማት ጉዞ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚህም ጥራትንና ፍጥነትን መመሪያ በማድረግ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በርካታ ፕሮጀክቶች ተቀርጸው ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ሥራዎች መሰራቱን ጠቅሰዋል። ፓርቲው የገባውን ቃልና የጀመራቸውን የልማት ሥራዎች ዳር ለማድረስ በቁርጠኝነት እየሰራ ውጤቱ በተጨባጭ እየታየ እንዳለ ተናግረዋል። በክልሉ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራትን ማከናወኑን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት ሦስት ዓመታት በሸገር ከተማ ዘመናዊ ከተማ የመገንባት ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም የመንገድ መሰረተ ልማቶ፣ የሆስፒታሎችና የትምህርት ቤቶች ግንባታን በማካሄድ ከፍተኛ የማኅበራዊ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል። እንዲሁም እንደሀገር የተቀረፁ የግብርና እና የኢኮኖሚ ዕቅዶችን በከተማ ደረጃ ስኬታማ ሥራ ለመስራት ማስቻሉን ተናግረዋል። ይህ ተግባርም ብልፅግና የሐሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባር የሚታዩ ሰፋፊ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ተናግረዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ጠቅላላ ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች በንቃት ሊሳተፉ ይገባል
May 23, 2026 874
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች የነቃ ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት እናታለም እንዳለ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር "በፖለቲካ፣ በምርጫና ሰላም ግንባታ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ማጎልበት" በሚል መሪ ሃሳብ ከማህበሩ አባላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል። የማህበሩ ፕሬዚዳንት እናታለም እንዳለ በዚሁ ወቅት፤ ማህበሩ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና እኩል ተሳታፊነትን የማረጋገጥ ዓላማ ይዞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሴቶች የመምረጥና የመመረጥ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በመንግስት አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ የነቃ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚያግዙ የአቅም ግንባታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 2 ሺህ 200 የማህበሩ አባል የሆኑ ሴቶች ሰልጥነው የታዛቢነት ፍቃድ መውሰዳቸውንም ጠቁመዋል። በተጨማሪም ሌሎችም ዕድሜያቸው ለምርጫ የደረሱ የማህበረሰብ ክፍሎች በምርጫው በመሳተፍ የሚመራቸውን መንግስት በድምፃቸው መምረጥ እንዲችሉ የማስገንዘብ ስራ እያከናውኑ መሆኑን ገልጸዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም ሴቶች በሃገር ሰላምና ፖለቲካ ውስጥ ያላቸውን የላቀ ፋይዳ በመገንዘብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድርሻቸውን እንዲወጡ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል። ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሴቶች የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል። የህብረተሰቡ ግንዛቤ ለማሳደግ ቤት ለቤት በመሄድና የተለያዩ መርሃግብሮችን በማዘጋጀት ለምርጫው አሳታፊነት የድርሻቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የገለጹት የማህበሩ አባል ወይዘሮ መሰረት ሶርሳ ናቸው። ወይዘሮ አዳነች አሉላ በበኩላቸው፤ ለምርጫ የደረሱ ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ በማስተማር የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ከ513 ሺህ በላይ አባላት እንዳለው ተመላክቷል።
ማህበራዊ
የምክክር ረቂቅ አጀንዳን ለባለድርሻ አካላት ማቅረብ እና ማስተቸት ለምን አስፈለገ?
May 25, 2026 48
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት ከሚኖሩ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አጀንዳ ሲያሰባስብ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ ኮሚሽኑ በዚህ ሂደት በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ባልተግባቡባቸው እጅግ መሠረታዊ የሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የምክክር አጀንዳዎቻቸውን እንዲሰጡ መደላድል ፈጥሯል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ኮሚሽኑ የተሰበሰበውን አጀንዳ አጠናክሮ እና ቀርፆ በማጠናቀቅ በምክክር ሀገራዊ መግባባት ሊደረግባቸው ያሻል ያላቸውን አዘጋጅቷል፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ኮሚሽኑ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔው ይመጥናሉ ብሎ የቀረፀውን ረቂቅ አጀንዳ ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት በማቅረብ ግብዓት በማሰባሰብ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ሂደት ለሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ብሎም ለአጀንዳ ቀረፃ የተለያዩ አበርክቶዎች እንደሚኖሩት የሚታመን ሲሆን የሚከተሉት ሃሳቦች ይህንን ያብራራሉ፡፡ 👉የአጀንዳ ሃሳቦች ትክክልኝነትን ከማረጋገጥ አንፃር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በርካታ ጉዳዮች በአጀንዳነት እንዲያዝላቸው ማቅረባቸውን ተከትሎ ያቀረቧቸው ሃሳቦች በምን ደረጃ ላይ እንዳሉ ለማወቅ ጉጉት ማሳደራቸው አጠያያቂ አይሆንም፡፡ በመሆኑም መሰል ተግባራት እና መድረኮች ኮሚሽኑ የባለድርሻ አካላትን አጀንዳ በአደራ ተረክቦ ሲቀርፅ በተፈለገው ቅርፅ ለታለመው ዓላማ መዘጋጀታቸውን ከእነዚሁ ባለድርሻ አካላት ጋር ማረጋገጡ ለምክክሩ ሂደት ጉልህ ሚናን ይጫወታል፡፡ 👉የሂደቱን ባለቤትነት ከማዳበር አንፃር የሀገራዊ ምክክር ረቂቅ አጀንዳን ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት አቅርቦ ማስተቸት እና በሂደቱ የእነዚህን አካላት ይሁንታ ለማግኘት መሻት ባለድርሻ አካላት በሂደቱ ላይ ያላቸውን የባለቤትነት መንፈስ ያጠናክርላቸዋል፡፡ ይህም ሁሉም አካላት በሂደቱ የሚኖራቸውን ሚና እንዲያጎለብቱ ያስችላቸዋል፡፡ 👉ግልፅነትን ከማጠናከር አንፃር ባለድርሻ አካላት በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሚመካከሩባቸውን የአጀንዳ ሃሳቦች ቀድመው ማወቃቸው እና ስለትክክለኛነታቸውም ይሁንታን መስጠታቸው ሂደቱን ግልፅ እና ተዓማኒ እንዲሆን ያግዘዋል፡፡ ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
በጋራ ዕውቀትና ዓላማ፣ይበልጥ ጤናማ የሆነች አፍሪካን አብረን መገንባታችንን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
May 24, 2026 653
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፦በጋራ ዕውቀትና ዓላማ፣ይበልጥ ጤናማ የሆነች አፍሪካን አብረን መገንባታችንን እንቀጥላለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፥ በኢትዮጵያ በልዩ የሕክምና ዘርፍ ሥልጠና ላይ ከሚገኙ እና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ከመጡ 400 በላይ የሕክምና ባለሙያዎች መካከል፤ከሩዋንዳ ከመጡ 128 የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በጋራ ማዕድ ቆርሰናል ሲሉ ገልጸዋል። እነዚህ ባለሙያዎች የአኅጉራችን የጤና ዘርፍ የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚጠይቀውን ከፍተኛ ዕውቀትና የላቀ ብቃት ለማሟላት ታምነው እየተጉ ያሉ መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ጠቁመዋል። ባለሙያዎቹ ቀጣዩን አፍሪካዊ ትውልድ በሕክምና ዘርፍ የሚኖረውን የመሪነት ሚና በማረጋገጥ ላይ የሚገኙ ተቋማት አካል ናቸው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም በጋራ ዕውቀትና ዓላማ፣ ይበልጥ ጤናማ የሆነች አፍሪካን አብረን መገንባታችንን እንቀጥላለን ነው ያሉት።
ለሁሉም የምትመች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ አዲስ የአርበኝነት ገድልን መጻፍ ይገባል - ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ታጋይ ታደለ
May 24, 2026 406
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፦ለሁሉም የምትመች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ አዲስ የአርበኝነት ገድልን መጻፍ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ፀሐፊ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ገለጹ። የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ "ሃይማኖታዊ እሴቶቻችን ለዘላቂ ሰላማችን" በሚል መሪ ሀሳብ ሀገር አቀፍ የአደባባይ የሰላም እና አብሮነት የጸሎት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ አካሂዷል። የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ፣ የሃይማኖት አባቶችና አባ ገዳዎች በመርሃ ግብሩ ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ፀሐፊ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የዓለም ተለዋዋጭ ሁኔታ ለሰው ልጆች እድል እና ፈተና ይዞ መምጣቱን በአግባቡ መረዳት ይገባል። ኢትዮጵያ ሁሉንም የምታሰባስብ ጥላ መሆኗን ገልጸው በውስጧ ያሉ ልዩነቶቿም አጥር ሳይሆን በህብረ ቀለም የደመቀ ውበት መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የዘመን ተሻጋሪ ጽኑ ታሪክ ባለቤት መሆኗን አውስተው፤ የኢትዮጵያዊነት ልዕልናው እና የማሸነፊያ ሚስጥር ቁልፉ በአባቶች እና በእናቶች ጸሎት መሆኑ የታሪክ ምስክር ነው ብለዋል። ሰላም የኔ ከምንለው አመለካከት እና ፍላጎት በላይ ናት ያሉት ዋና ፀሐፊው፤ አንድነትን እና ሰላምን ለማጽናት ሳያቋርጡ በጸሎት መትጋት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር እንደሚገባ አመላክተው፤ ጸሎት የልብ ትስስርን ለመፍጠር የሚረዳ የመንፈስ አንድነትን የሚገነባ ድልድይ መሆኑን ጠቁመዋል። ለሁሉም የምትመችና የምትበቃ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ አዲስ የአርበኝነት ገድልን መጻፍ እንደሚገባ አመላክተዋል። በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር በአንድነት ለሀገር ሰላም እና እድገት መስራት እንደሚያስፈልግ ያመለከቱት ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ታጋይ፤ በሥራ በመጠንከርና በመትጋት ድህነትን መዋጋት አለብን ነው ያሉት። በበጎ የሚወሳ አሻራ ለማኖር የአባቶቻችንን አደራ እንወጣ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
አርብቶ አደሩ አካባቢ የተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን የሚያሳድጉ ናቸው
May 24, 2026 431
ሰመራ፣ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡- በአርብቶ አደሩ አካባቢ የተገነቡ የልማት ፐሮጀክቶች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን የሚያሳድጉ መሆኑን የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኀላፊ ኡመር ኑር ገለጹ። በቂልበቲ ረሱ ዞን መጋሌ ወረዳ የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀው ወደ ስራ ገብተዋል። ከተመረቁት ፕሮጀክቶች ውስጥ በ10 ሚሊየን ብር የተገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋም ይገኝበታል። የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኀላፊ አቶ ኡመር ኑር በወቅቱ እንደገለጹት በአርብቶአደሩ አካባቢ የተገነቡ የልማት ፐሮጀክቶች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን የሚያሳድጉ ናቸው። በተለይም የመጠጥ ውሃ ግንባታው እናቶች ውሃ ፍለጋ የሚያደርጉትን ረጅም ጉዞ በማስቀረት ጉልበትና ጊዜያቸውን በልማት ለማዋል እንደሚያስቻላቸው ተናግረዋል። በቀጣይም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለሚያደርጉ ፕሮጀክቶች ትኩረት እንደሚሰጥ አመላክተዋል። የአፋር ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኀላፊ አቶ አህመድ ሻሚ በበኩላቸው ለአርብቶ አደሩ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽ ለማድረግ ከአጋር አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። አሁን ላይ ለምረቃ የበቃው የውሀ ፕሮጀክትም በፀሃይ ሐይል የሚሰራና የወረዳውን የንፁህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት የሚያሻሽል መሆኑን ገልጸዋል። የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋሙን ለመገንባት 10 ሚለየን ብር ወጭ መደረጉን ተናግረዋል። የመጋሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱ ሸኸበራ በበኩላቸው ዛሬ የተመረቀው የውሀ ፕሮጀክት ለህብረተሰቡ የመጠጥ ውሀ አቅርቦት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን አንሰተዋል። የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋሙ ለረጅም ጊዜ አገልግልት እንዲሰጥ ህብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስበዋል። በእለቱ እድሳት የተደረገላቸው ጤና ጣቢያ፣ ትምህርት ቤትና ሌሎች አገልግሎት መስጫዎች ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል።
ኢኮኖሚ
በክልሉ የአርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስገኙ ነው
May 24, 2026 395
ነገሌ ቦረና፣ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የአርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስገኙ መሆናቸው ተገለጸ። በምስራቅ ቦረና ዞን ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነቡ የፊና መስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹን የመረቁት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማእረግ የማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻህ ናቸው፡፡ የክልሉ መንግስት የአርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የቆላማና ዝናብ አጠር አካባቢዎች ዘላቂ ልማት እቅድ በመንደፍ የድርቅ ተጋላጭነትን ለመቋቋም እየሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን የማጠናከር፣ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራና የበጋ መስኖ ልማትን በመተግበር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሰራቱን አንስተዋል። በክልሉ የቆላማ አከባቢዎች የአርብቶ አደሩን የመስኖ ልማትን ለማጠናከርና የእንስሳት መጠጥ ወሀ አቅርቦት ችግር ለመፍታት የፊና ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግም ጥረት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በምስራቅ ቦረና ዞን ዛሬ ለምርቃት የበቁት ፕሮጀክቶችም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ለማሳካትና ለእንስሳት ውሀ አቅርቦት ይውላሉ ብለዋል፡፡ በቀጣይም የክልሉ መንግስት ተመሳሳይ ፕሮጀክቶችን ለውጤት በማብቃት የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያደረገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል፡፡ የክልሉ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ኢንጅነር አለሙ ረጋሳ በምስራቅ ቦረና ዞን የአርብቶ አደሩን የመሰረተ ልማት ተደራሽነት ለማረጋገጥ በግንባታ ላይ ከነበሩ ሶስት የፊና መስኖ ፕሮጀክቶች መካከል ሁለቱ ለአገልግሎት መብቃታቸውን ጠቁመዋል። በዞኑ ሊበንና ጎሮ ዶላ ወረዳ በግንባታ ላይ ከነበሩት ሁለቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹም በቆላማና ዝናብ አጠር አከባቢዎች የሚታየውን የድርቅ ተጋላጭነት በዘላቂነት ለመቋቋም፣ ለበጋ መስኖ ስንዴ ልማትና ለእንስሳት መጠጥ ውሀ አቅርቦት እንዲሁም ለመኖ ልማት እንደሚውሉ አመላክተዋል። የክልሉ መንግስት ግንባታቸው ለተጠናቀቁት የፊና መስኖ ፕሮጀክቶች 518 ሚሊዮን ብር ወጭ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ የመስኖ ፕሮጀክቶቹ 8 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሜትር ኪውብ የዝናብ ውሀ የመያዝ አቅም ያላቸው እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡ የምስራቅ ቦረና ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱረዛቅ ሁሴን በበኩላቸው ፕሮጀክቶቹ ከ465 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ የማልማት አቅም አላቸው ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ አርብቶ አደሩን በመስኖ ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር ከቀየው ሳይርቅ ለእንስሳቱ የመጠጥ ውሀ እንዲያገኝ የሚያስችሉት መሆኑን አመልክተዋል። በዞኑ የሊበን ወረዳ ነዋሪ አቶ ቃሲም ገመዳ በበኩላቸው የፕሮጀክቶቹ መገንባት የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎች የመለሱ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ በአካባቢው የተሰሩት የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች ቀደም ሲል ለእንስሳት መኖና የመጠጥ ውሀ ፍለጋ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንደሚያስቀሩላቸው ተናግረዋል።
በክልሉ በፍራፍሬና በቡና ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል − ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
May 24, 2026 322
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በፍራፍሬ እና በቡና ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ በክልሉ በፍራፍሬ፣ በቡናና ሥራስር ተክሎች ልማት ለሀገር ውስጥ እና ለውጪ ገበያ ለማቅረብ የተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቶባቸዋል። በዚህም ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች ላይ ይበልጥ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በበጋ መስኖና በመኸር እርሻ ከ107 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በፍራፍሬና በአትክልት መሸፈኑን ተናግረዋል። በዋናነትም ሙዝ፣ ማንጎ፣ አቮካዶ እና የደጋ ፍራፍሬ እንዲሁም የተለያዩ የጓሮ አትክልቶች መልማታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። ከሀገራዊ ለውጡ በፊት በክልሉ ከ60 ሺህ ሄክታር ያልበለጠ የሙዝ ማሳ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ጥላሁን፣ በአሁኑ ወቅት በአራት እጥፍ አድጎ ከ240 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር ለፍራፍሬ ልማት ሽፋን እያደገ መምጣት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ገልጸዋል። እንደ አቶ ጥላሁን ገለጻ በተያዘው ዓመት በፍራፍሬ የሚለማውን መሬት ሽፋን ለማሳደግ በተያዘ ዕቅድ በተለያዩ አካባቢዎች የሚተከሉ ከ25 ሚሊዮን በላይ የአቮካዶ፣ ማንጎ እና አፕል ችግኞች ተዘጋጅተዋል። በማህበር የተደራጁ ወጣቶችም በፍራፍሬ ልማት፣ በግብይትና ማቀነባበር የሥራ ዕድል ተፈጥሮላቸው ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ነው የገለጹት። የቡና ልማትን ከማስፋፋት አንጻር ለቡና ምቹ በሆኑ ሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ልማቱ እየተከናወነ መሆኑን ያመለከቱት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በጌዴኦ ዞን ቡናን ስፔሻላይዝድ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። የቡና ልማቱን በጥምር ግብርና በማከናወን የአርሶ አደሩን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራትም ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። በክልሉ የቡና ልማቱን ለማስፋት በተያዘው ዕቅድ መሰረት ዘንድሮ ከተዘጋጁ የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው የቡና ችግኞች አብዛኞቹ ባለፈው ሚያዝያ ወር መተከላቸውን ገልጸው፣ ቀሪዎቹ በቀጣይ ሐምሌ ወር ይተከላሉ ብለዋል።
በአማራ ክልል የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ የሚያጠናክሩ ተግባራት ትኩረት የተሰጣቸው ናቸው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
May 24, 2026 251
ጎንደር ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ የሚያጠናክሩ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ አስታወቁ ። የጎንደር የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት በጎንደር ዙሪያ ወረዳ ዛሬ ተካሂዷል ። ርእሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚያጠናክሩና የሚያሳልጡ ተግባራት ትኩረት የተሰጣቸው ናቸው ። በክልሉ ግንባታው የተጀመረው የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የዚሁ አካል መሆኑን ጠቁመው ፓርኩ በክልሉ ዋነኛ የኢኮኖሚ ማእከል እንደሚሆንም አመልክተዋል ። የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በበኩላቸው በሀገሪቱ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር በማፋጠን ረገድ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወሳኝ የእድገት ምሰሶዎች ናቸው ብለዋል። የተቀናጀ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የግብርና ምርት እሴት ጨምሮ ለሀገርና ለውጪ ገበያ ለማቅረብ ምቹ የኢኮኖሚ መሠረት የሚጥሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዛሬ ግንባታው የተጀመረው አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የአካባቢውን የግብርና ምርት በስፋት በመጠቀም ለአካባቢው አምራች አርሶ አደሮች ሰፊ የገበያ እድል የሚፈጥር እንደሆነም አመልክተዋል። ፓርኩን በሂደት ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በማሳደግ እንደ ሀገር ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን ሽግግር ለማሳለጥ ምቹ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰዋል። ፓርኩ ለግብርና ምርቶች የገበያ እድል በማመቻቸት ለወጣቶች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም ለከተሞች ገቢ ማደግና ለቴክኖሎጂ ሽግግር የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለውም ጠቁመዋል። የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሀኑ ጣምያለው ኢንዱስትሪ ፓርኩ በ256 ሄክታር መሬት ላይ ግንባታው እንደሚካሄድ ገልጸዋል። የፓርኩ ግንባታ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ የኢንቨስትመንት ወጪ እንደሚጠይቅ ጠቁመው ስራ ሲጀምር ለ55 ሺህ ወገኖች ቋሚ እንዲሁም ከ200ሺህ በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ጊዚያዊ የስራ እድል ይፈጥራል ብለዋል። ፓርኩ በአመት ከአንድ ሚሊዮን ቶን በላይ ምርት የማቀናበር አቅም ሲኖረው እሴት የተጨመረባቸውን ምርቶች ለውጪ ገበያ በማቅረብ የውጪ ምንዛሪ የሚያስገኝ መሆኑንም አስታውቀዋል። የማእከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ ዞኑ ለአግሮ ኢንዱስሪዎች ግብአት የሚውል ሰሊጥ፣ አኩሪ አተርና ጥጥ የመሳሰሉ የግብርና ምርቶች በስፋት የሚመረቱበት እንደሆነ ተናግረዋል ። ኢንዱስትሪ ፓርኩ ለአካባቢው የኢኮኖሚ መነቃቃት አስተዋፅኦው የላቀ መሆኑንም አመልክተዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኩ የግንባታ ማስጀመሪያ ስነ ስርአት ላይ የፌደራል፣ የክልል እንዲሁም የጎንደር ከተማና የማእከላዊ ጎንደር ዞን አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ ተገኝተዋል።
በሐረሪ ክልል አቮካዶን በተሻለ ደረጃ በማምረት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ወደ ስራ ተገብቷል
May 24, 2026 235
ሐረር፣ ግንቦት 16/2018(ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል የአቮካዶ ልማትን በተሻለ ደረጃ በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ወደ ስራ መገባቱን የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ አስታወቀ። በኢትዮጵያ ከፍተኛ የገበያ ተፈላጊነት ያላቸውንና አምራች አርሶ አደሮችን በአጭር ጊዜ ተጠቃሚ የሚያደርጉ እንደ አቮካዶ ያሉ ከፍተኛ እሴት ያላቸው አትክልትና ፍራፍሬ ልማቶች በስፋት እየተስፋፉ ይገኛሉ። የሐረሪ ክልልም ያለውን የተወሰነ የእርሻ መሬት በቴክኖሎጂ በማገዝ ምርታማነትን ለመጨመርና የአካባቢውን ማህበረሰብ የውስጥ ፍጆታ ከመሸፈን ባለፈ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ያቀደውን ስራ ስኬታማ ለማድረግ፣ የአመራሩና የባለሙያው አቅም መገንባት ወሳኝ መሆኑ ይገለጻል። በክልሉ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም ለማስጀመር በልማቱ ዙሪያ ለዘርፉ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ነስረዲን አህመድ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ ከአረንጓዴ አሻራ ልማት ጋር በማያያዝ አቮካዶን የማልማት ስራ እየተከናወነ ነው። ይህንን ተግባር ለማጎልበት በክልሉ በብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም የተለያዩ ስራዎች ተቀርጸው ተግባራዊ የማድረግ ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። በዚህም የአቮካዶ ልማት የሚከናወንበት ቦታን የመለየት ስራ መከናወኑን የተናገሩት አቶ ነስረዲን በክልሉ በአራቱ የገጠርና ከተማ ወረዳዎች ውስጥ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተናግረዋል። በተለይም የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የአቮካዶ ልማት የዝግጅት ስራዎች አንዱ መሆኑን ጠቁመው ችግኝ የማፍላትና የማዳቀል እንዲሁም የአርሶ አደሮችን ግንዛቤ የማሳደግ ስራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል። ይህ የአቮካዶ ልማት ኢንሼቲቭ በቴክኖሎጂ በማዘመን አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ፣ ምርቱን ለዓለም አቀፍ ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬን ማሳደግ እንዲሁም በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። የሐረሪ ክልል አየር ፀባይ ለአቮካዶ ልማት ምቹ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ መሐመድ ሬድዋን ናቸው። ይህ ፕሮግራም በክልሉ ምርትና ምርታማነትን በማጎልበት የአርሶ አደሩን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ሥራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ እገዛ ከማድረጉ ባለፈ ለወጣቶችም የስራ እድል ይፈጥራል ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የአፈር ለምነትን በዘላቂነት የሚጠብቁ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮች እየተጠናከሩ ነው
May 23, 2026 729
አምቦ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ የአፈር ለምነትን በዘላቂነት የሚጠብቁ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን በመተግበር ምርታማነትን ለመጨመር የሚያስችሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል አዲስ በአፈርና ውሃ ላይ ጥናትና ምርምር ለማድረግ የሚያግዝ ላብራቶሪ ስራ አስጀምሯል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ንጉሤ ደቻሳ (ፕ/ር) እንደገለጹት፤ የአፈር ለምነትን መጠበቅ ለምርትና ምርታማነት እድገት መሰረታዊ በመሆኑ፣ የአፈር ለምነትን የሚቀንሱ ችግሮችን በሳይንሳዊ ዘዴ መለየትና የላብራቶሪ ማዕከላትን ማጠናከር አስፈልጓል። በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ዛሬ ተመርቆ ስራ የጀመረው የአፈር እና ውሃ ላብራቶሪም የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የላብራቶሪው ዋና ዓላማም የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማድረግና የግብርናውን ዘርፍ ማሳደግ እንደሆነ አንስተዋል። የአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ጀማል ቶላ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ባለፉት ዓመታት ከአካባቢው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ለእጽዋት ጥበቃ የሚውሉ ሳይንሳዊ የምርምር ውጤቶችን ሲያቀርብ መቆየቱን ተናግረዋል። የምርት መጠንን ለመጨመር የሰብል ልማትን የሚደግፉ ሰፋፊ የግብርና ምርምሮች እየተካሄዱ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ይህም የአካባቢውን አርሶ አደሮች ከመደገፍ ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ዘርፈ-ብዙ ስራዎች እንዲከናወኑ ማድረጉን ተናግረዋል። ማዕከሉ ግብርናን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ፣ የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችንና የግብርና ግብዓቶችን በማቅረብ የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። የአምቦ ወረዳ አርሶ አደር ወይዘሮ እሸቱዋ ሚደቅሳ በበኩላቸው፤ ከግብርና ማዕከሉ ባገኙት ስልጠና በመታገዝ የተሻሻለ የበቆሎ ዝርያ ወስደው በመዝራታቸው፣ ምርታቸው ከበፊቱ እጥፍ መጨመሩን ተናግረዋል።
የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በክህሎት የበለፀገ የሰው ኃይል በማፍራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን እያሳለጠ ነው
May 23, 2026 457
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በክህሎት የበለፀገ የሰው ኃይል በማፍራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን እያሳለጠ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መርሃ ግብር እስከ አሁን ከ4 ነጥብ 85 ሚሊየን በላይ ሰዎች ስልጠና በመውሰድ የሰርተፍኬት ባለቤት እየሆኑ እንደሚገኝም አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ስልጠናን ሐምሌ 2016 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው የሚታወስ ነው። የአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ተነሳሽነት ወጣቶች ላይ ትልቅ ለውጥ ለማምጣት ያለመ የዲጂታል ክህሎት ማልሚያ መርሃ ግብር ሆኖ እያገለገለ ሲሆን በዚህም ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገብ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግሥት ጋር በመተባበር ያስጀመረው የኢትዮ-የኮደርስ ስልጠናም ሀገራዊ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን በማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። ስልጠናውም ዜጎች በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ዳታ አናሊሲስ፣ በአንድሮይድና በፕሮግራሚንግ ዴቨሎፕመንት ዋና ዋና ዘርፎች ስልጠና የሚያገኙበትን ምኅዳር ፈጥሯል። ስልጠናው በኦላይን ሥርዓት በነፃ የሚሰጥና ዜጎች ያለ ዕድሜ ገደብ መሠረታዊ የዲጂታል ስልጠና ወሰደው ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለው ሰርተፍኬት ያገኙበታል። የዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓትን በመገንባት ሂደትም በርካታ ዜጎችን የቴክኖሎጂ ክህሎት በማስታጠቅ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል። ይህም የኢትዮጵያን የግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ብዝኅ የኢኮኖሚ ጉዞ የሚያሳልጥ ሀገር በቀል የዲጂታል ክህሎት የታጠቀ ትውልድ በማፍራት እያስቻለ ነው። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ስዩም መንገሻ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዲጂታል ኢኮኖሚን መገንባት የሚያስችል ሥነ-ምኅዳር ተፈጥሯል። ለአብነትም የአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በርካታ ዜጎች የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት የሚታጠቁበትን አስቻይ የአሰራር ሁኔታ መፍጠሩን አስታውቀዋል። የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ከተጀመረ አንስቶም እስካሁን ከ4 ነጥብ 85 ሚሊየን በላይ ዜጎች የስልጠናው አካል በመሆን የተለያዩ የዓለም አቀፍ ሰርተፊኬት ባለቤት እየሆኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለፈጠራና ቴክኖሎጂ ልማት የተሰጠው ትኩረትም የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያሳልጥ የሰው ሃይል ማፍራት እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠናም የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት የታጠቀ ብቁ የሰው ሃይል በማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አንስተዋል። የስልጠና መርሃ ግብሩም ዜጎች ባሉበት ቦታ ሆነው በኦላይን ሥርዓት ዕውቀት የሚሸምቱበትን ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል። በቀሪ የሥልጠናው ጊዜያትም ዜጎች የዕድሉ ተጠቃሚ በመሆን የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት ማዳበር እንደሚችሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በማረጋገጥ የሳይበር ደኅንነት ስጋትን የሚቀለብስ የሰው ሃይል ማፍራት እየተቻለ ነው
May 21, 2026 1005
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በማረጋገጥ የሳይበር ደኅንነት ስጋትን የሚቀለብስ የሰው ሃይል ማፍራት እየተቻለ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ገለጸ። አስተዳደሩ በዘንድሮው ክረምት ለ5ኛ ጊዜ የሚያካሂደውን የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ (Cyber Talent Summer Camp) ዝግጅት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። የአስተዳደሩ የሳይበር ልህቀት ማዕከል ዳይሬክተር ቢሻው በየነ በመግለጫቸው፤ መርሃ ግብሩ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች በማሰልጠን የሳይበር ደኅንነትና የቴክኖሎጂ ሙያተኞችን ለማፍራት ያለመ ነው ብለዋል። የስልጠና መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያን የሳይበር ደኅንነትና ሉዓላዊነት የማስጠበቅ አቅምን የበለጠ ለማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ ኢትዮጵያ በዘርፉ ሀገራቸውን ከሳይበር ጥቃት የሚከላከልና ብቁ የሳይበር ሠራዊት ማፍራት መሆኑን አብራርተዋል። እንደ እስራኤል፣ እንግሊዝ እና አሜሪካ ያሉ ሀገራት ተሞክሮ መርሀግብሩ ታዳጊዎችን ለማፍራት ያለውን ወሳኝነት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። ይህ ካምፕ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግና የኢትዮጵያን ዲጂታል ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል። የዘንድሮው የስልጠና ካምፕ በክልል ደረጃ በስድስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲካሄድ የተወሰነ ሲሆን ይህም ታዳጊዎች በቅርበት ስልጠናውን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል። በእስካሁኑ ሂደትም ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ከ4 ሺህ በላይ ታዳጊዎችና ወጣቶች መመዝገባቸውን ገልፀዋል። ምዝገባውም ግንቦት 17/2018 ዓ.ም የሚጠናቀቅ በመሆኑ በሳይበር ደህንነትና ቴክኖሎጂ ልዩ ተሰጥኦና ፍላጎት ያላቸው ታዳጊዎችና ወጣቶች በኦንላይን እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
የምርት ጥራት ደረጃ ማረጋገጫ መተግበሪያው የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው
May 21, 2026 671
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018(ኢዜአ)፦ የምርት ጥራት ደረጃ ማረጋገጫ መተግበሪያው የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት አፈጻጸም ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በዛሬው ዕለት የምርት ጥራት ደረጃን በኦንላይን ማረጋገጥ የሚያስችል መተግበሪያ አስመርቆ ወደ ስራ አስገብቷል። በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሠረት በቀለ (ዶ/ር) ተገኝተዋል፡፡ ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርሙ በንግድ ስርዓቱ ላይ ትልቅ እመርታ እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከ46 በላይ አገልግሎቶች በኦንላይን እየተሰጡ እንደሚገኙ ጠቅሰው፥ ይህም የንግድ ሥርዓቱን በማዘመን የምርት ጥራት አፈፃጸም ላይ የላቀ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት አስር ወራት ብቻ ከወጪ ንግድ ከ8 ነጥብ 7 ቢሊየን በላይ የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱንም ነው የተናገሩት፡፡ ዛሬ የተመረቀው የኦንላይን መተግበሪያ አገልግሎቶችንና የምርት ጥራትን በላቀ አፈፃጸም መምራት የሚያስችል መሆኑንና የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት አፈፃጸም ውጤታማነት ለማላቅ አይነተኛ ሚና ያበረክታል ብለዋል። የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሠረት በቀለ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ተስፋ ሰጭ የለውጥ ጉዞ እያስመዘገበች ትገኛለች ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ የለውጥ ጉዞውን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሕግና ተቋማዊ ማሻሻያዎችን እንዳደረገ በመግለጽ፡፡ የዚህ ጥረት አካል የሆነው የኦንላይን የምርት ጥራት ማረጋገጫ መተግበሪያ የኢትዮጵያ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ በዋጋና በጥራት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑንም አክለዋል፡፡ መተግበሪያው የኢንስቲትዩቱን የማስፈጸም አቅም ሀገሪቱ ከደረሰችበት የዕድገት ደረጃ ጋር እንዲጣጣም አጋዥ ስለመሆኑም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በምርት ጥራት ላይ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ እንደሚሆኑ የተናገሩት ደግሞ የአፍሪካ የደረጃዎች ተቋማት የማዕከላዊ ኮሚቴ ጸሐፊ ሬዩበን ጊሶር ናቸው፡፡ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወናቸውን አጠቃላይ ተቋማዊ የሪፎርም ስራዎችን አስመርቋል።
ስፖርት
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከመቀሌ 70 እንደርታ ለኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ለማለፍ ይጫወታሉ
May 25, 2026 78
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዋንጫ የመጀመሪያ የግማሽ ፍፃሜ መርሐ ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከመቀሌ 70 እንደርታ ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ጨዋታው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በሩብ ፍጻሜው መቻልን በመለያ ምት በማሸነፍ አራት ውስጥ ገብቷል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በበኩሉ በሩብ ፍጻሜው ቦዲቲ ከተማን 3 ለ 2 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። ሁለቱ ቡድኖች በዘንድሮው የውድድር ዓመት ለሶስተኛ ጊዜ ይገናኛሉ። በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሊጉ ሁለት ጊዜ ተገናኝተው በተመሳሳይ አንድ አንድ ጊዜ አሸንፈዋል። ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተገናኝተው መቀሌ 70 እንደርታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ፍፁም አለሙ እና ኮትዲቯራዊው አብዱላጢፍ ባምባ የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ዳዊት ገብሩ ለወልዋሎ ግቧን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በፕሪሚየር ሊጉ በ40 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በ34 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። የጨዋታው አሸናፊ ቡድን በፍጻሜው ከሲዳማ ቡና እና ኢትዮጵያ መድን አሸናፊ ጋር ይጫወታል።
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ቀን ውሎ
May 24, 2026 477
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ማምሻውን ተጠናቋል። ሁሉም የ38ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሰዓት ተደርገዋል:: የሻምፒዮኖቹ አርሰናል የድል ፌሽታ ሲያነሳ፣ የጎረቤቱ ቶተንሃም ከመውረድ መትረፍ፣ የዌስትሃም ከሊጉ መሰናበት፣ የሊቨርፑል የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ማረጋገጥ እና የብሩኖ ፈርናንዴዝ አዲስ ክብረ ወሰን፤ እለቱን በክስተቶች የታጀበ አድርጎታል። በሳምንቱ አጋማሽ ከ22 ዓመታት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋገጠው አርሰናል ለረጅም ጊዜ የናፈቀውን ዋንጫ በደማቅ ስነ ስርዓት አንስቷል። መድፈኞቹ በሰልኸረስት ፓርክ ባደረጉት ጨዋታ ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 አሸንፈዋል። ጋብርኤል ጄሱስ እና ኖኒ ማዱዌኬ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጂን ፍሊፕ ማቴታ የፓላስን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። አርሰናል በ85 ነጥብ ዓመቱን በአንደኝነት ተጠናቋል። ከጨዋታው በፊት የክሪስታል ፓላስ ተጫዋቾች በግራ እና በቀኝ በመቆም ለሻምፒዮኑ አርሰናል የክብር አቀባበል (Guard of honour) አድርገዋል። ተከታዩ ማንችስተር ሲቲ በአስቶንቪላ የ2 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል። ኦሊ ዋትኪንስ ለቪላ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥሯል። አንቶዋን ሴሜኒዮ የሲቲን ጎል ከመረብ አገናኝቷል። ሲቲ በ78 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። የውሃ ሰማያዊዎቹ አሰልጣኝ ፔፔ ጋርዲዮላ ከጨዋታው በኋላ ክለቡን በይፋ ተሰናብቷል። በርናንዶ ሲልቫም ሲቲን ተሰናብቷል። የማንችስተር ሲቲው አርሊንግ ሃላንድ በ27 ጎሎች የሊጉ ኮከብ ግብ አስቆጣሪ በመሆን ተጠናቋል። በሊጉ የመዝጊያ ቀን ሲጠበቁ ከነበሩ ጉዳዮች መካከል አንዱ ላለመውረድ የሚደረግ ትግል ነው። ቶተንሃም ሆትስፐርስ በሜዳው ኤቨርተንን አስተናግዶ 1 ለ 0 በማሸነፍ በ41 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል። ጆአኦ ፓሊኒያ የስፐርስን ብቸኛ ጎል አስቆጥሯል። ዌስትሃም ዩናይትድ ሊድስ ዩናይትድን 3 ለ 0 ቢያሸንፍም ከሊጉ ወርዷል። ቫለንቲን ካስቴላኖስ፣ጃሬድ ቦወን እና ካሉም ዊልሰን ግቦቹን አስቆጥረዋል። ዌስትሃም ዩናይትድ በ39 ነጥብ 18ኛ ደረጃን በመያዝ ከሊጉ ተሰናብቷል። የለንደኑ ክለብ ከ14 ዓመታት የሊጉ ቆይታ በኋላ ወደ ሻምፒዮንሺፑ ወርዷል። ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ አንድ አቻ በመለያየት በ60 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን አረጋግጧል። መሐመድ ሳላህ እና አንዲ ሮበርትሰን ከጨዋታው በኋላ ሊቨርፑልን በይፋ ተሰናብተዋል። ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በመርታት በ54 ነጥብ የዩሮፓ ሊግ ተሳታፊነት ትኬቱን ቆርጧል። ቦርንማውዝ ሌላኛው የዩሮፓ ተሳታፊ ክለብ ነው። ቡዱኑ ዛሬ ከኖቲንግሃም ፎረስት ጋር አንድ አቻ በመለያየት በ57 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። ቼልሲ በ52 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዞ በመጨረስ ከአውሮፓ መድረክ ተሳትፎ ውጪ ሆኗል። ማንችስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 አሸንፏል። በአሜክስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፓትሪክ ዶርጉ፣ ብሪያን ምቡዌሞ እና ብሩኖ ፈርናንዴዝ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ለዶርጉ ጎል መቆጠር እጁ የነበረበት ብሩኖ ፈርናንዴዝ በዓመቱ 21 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል። ከዚህ ቀደም ቲዬሪ ሄነሪ እና ኬቨን ደ ብሮይን (በተመሳሳይ 20 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል) በጣምራ ይዘው የነበሩትን ክብረ ወሰን አሻሽሏል። ፈርናንዴዝ ትናንት የሊጉ የዓመቱ ምርጣ ተጫዋች በመባል መመረጡ አይዘነጋም። ዩናይትድ በ71 ነጥብ ሶስተኛ ሆኖ ዓመቱን አጠናቋል። ብራይተን በ53 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በኮንፍረንስ ሊግ መሳተፉን አረጋግጧል። ፋልሃም ኒውካስትል ዩናይትድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ወራጆቹ በርንሌይ እና ዎልቭስ ባደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይተዋል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እስከ መጨረሻው ደቂቃ በድራማ እና ትዕይንቶች ታጅቦ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ ከ 17 ዓመት በታች ሴት ብሔራዊ ቡድን የቡሩንዲ አቻውን 2ለ1 አሸንፏል
May 24, 2026 329
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ከ 17ዓመት በታች ሴት ብሔራዊ ቡድን ከቡሩንዲ ያደረገውን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ጨዋታ 2ለ1 አሸንፏል። አበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ለቡድኑ የማሸነፊያ ሁለት ግቦችን ሊዲያ እያሱ ማስቆጠር ችላለች። ኢትዮጵያ በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ዙር ማጣሪያ ደቡብ ሱዳንን በድምር ውጤት 8 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፉ ይታወቃል። ተጋጣሚዋ ብሩንዲ በመጀመሪያው ዙር ማላዊን በአጠቃላይ ውጤት 4 ለ 2 አሸፋለች። የሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታው ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ቡጁምቡራ ላይ ይካሄዳል። ኢትዮጵያ በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈች ለመጨረሻው ዙር ማጣሪያ ትጫወታለች። 10ኛው የፊፋ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የማጣሪያ ጨዋታውን ከብሩንዲ ጋር ያከናውናል
May 24, 2026 303
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፦ በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ የሁለተኛ ዙር ማጣሪያ ኢትዮጵያ ከብሩንዲ ጋር ዛሬ የመጀመሪያ ጨዋታዋን ታደርጋለች። የሁለቱ ሀገራት ጨዋታ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይካሄዳል። ኢትዮጵያ በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ዙር ማጣሪያ ደቡብ ሱዳንን በድምር ውጤት 8 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፉ ይታወቃል። ተጋጣሚዋ ብሩንዲ በመጀመሪያው ዙር ማላዊን በአጠቃላይ ውጤት 4 ለ 2 አሸፋለች። አሰልጣኝ ራውዳ አሊ ለማጣሪያ ጨዋታው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለ30 ተጫዋቾች ጥሪ ካደረጉበት ጊዜ አንስቶ ብሔራዊ ቡድኑ ልምምዱን ሲያደርግ ቆይቷል። ራውዳ የመጀመሪያ ጥሪ ከተደረገላቸው 30 ተጫዋቾችች መካከል አምስቱን በመቀነስ ቡድኑ ዝግጅቱን ቀጥሏል። ብሔራዊ ቡድኑ የመጨረሻ ልምምዱን ትናንት በአበበ በቂላ ስታዲየም ማድረጉንና ተጫዋቾች በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በፓትሪክ ሳንጋዋ የሚመራው የብሩንዲ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከኢትዮጵያ ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል። የሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታው ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ቡጁምቡራ ላይ ይካሄዳል። ኢትዮጵያ በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈች ለመጨረሻው ዙር ማጣሪያ ትጫወታለች። 10ኛው የፊፋ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ 24 ሀገራት ይሳተፋሉ። በዓለም ዋንጫው አፍሪካ ሞሮኮን ጨምሮ በአምስት ሀገራት ትወከላለች። በማጣሪያ የሚያልፉ አራት የአፍሪካ ሀገራት በሶስት ዙሮች በሚደረጉ ጨዋታዎች ይለያሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለቀጣናው ብልፅግና የላቀ ሚና አለው
May 23, 2026 613
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር እንዲሁም ብልፅግናን ለማጎልበት የላቀ ሚና እንዳለው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሰላምና ደህንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የራሷን የተፈጥሮ ሀብት ከመንከባከብ ባለፈ፣ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የሚከሰቱ አደጋዎችን በጋራ ለመከላከል የአካባቢውን አገራት አብሮ የመልማት ዕቅድ ይዛ እየሠራች ስለመሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህም በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለጎረቤት አገራት በርካታ ችግኞችን ማበርከቷ ይታወቃል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የሚከሰቱ የተፈጥሮ መዛባቶችን ለመከላከል፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና አካባቢን ለመታደግ ታስቦ በከፍተኛ ሀገራዊ ቁርጠኝነት እየተተገበረ የሚገኝ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው። ይህ ንቅናቄ በአገር ውስጥ ካስገኛቸው ሁለንተናዊ ጥቅሞች ባሻገር፣ ለጎረቤት አገራትና ለጠቅላላው የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትስስር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ የምታከናውነው የተፈጥሮ ጥበቃ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለቀጣናው አገሮች የሚተርፍ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ነው፡፡ የኢጋድ ሰላምና ደህንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በቀጣናው እንደ ጎርፍ፣ የበረሃ አንበጣ እና ድርቅ ያሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎች የሰዎችን መፈናቀልና ስደት ይፈጥራሉ፡፡ በዚህም ዜጎች ከአካባቢያቸው ችግሩ ወደ ሌለባቸው አካባቢዎችና ድንበሮችን አቋርጠው የሚሰደዱበትን ሁኔታ የሚፈጠር ሲሆን፤ ይህም በቀጣናው ላይ የሚያሳድረው ጫና ቀላል እንዳልሆነ አመልክተዋል። ይህንን ተግዳሮት ለመቋቋም በኢትዮጵያ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ውጤቶችን እያሳየ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ አሁን ላይ የሚታየው መደበኛ የዝናብ ሁኔታ ስኬት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ተከትሎ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እየተጠናከረ በሄደ ቁጥር በቀጣናው የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር፣ ሰላምና ብልፅግናን ለማጎልበት የራሱ የሆነ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው አንስተዋል። ይህንን የኢትዮጵያን መልካም ተሞክሮ በመረዳት እንደ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ጅቡቲ ያሉ የጎረቤት አገራት ተመሳሳይ አረንጓዴ ልማቶችን እየተከተሉ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ከዋና ዋና ዓላማዎቹ መካከል አንዱ የግብርና እና የአካባቢ ጥበቃ ልማት መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ ይህንን የኢትዮጵያን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ሀሳብ በጽኑ እንደሚደግፈው ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ባለፉት ዓመታት በከፍተኛ ተነሳሽነት ሲተገበር ቆይቷል። በመርሀግብሩ እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ጉልህ ድርሻ እየተጫወተ ይገኛል። ይህ ግዙፍ ብሔራዊ የልማት ፕሮጀክት በኅብረተሰቡ ዘንድ ችግኞችን የመትከልና የመንከባከብ በጎ ባህል እንዲዳብርና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤ እንዲያድግ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል። በተለይም በችግኝ ማፍላት፣ በተከላና ተያያዥ ሥራዎች ላይ ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር በሀገሪቱ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ላይ አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎችን ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ
May 22, 2026 888
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 14/2018 (ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎችን ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች በርካታ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ ስፍራዎች ላይ ለዝናብ መፈጠር አመቺ የሆኑ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች አንጻራዊ ጥንካሬ ይኖራቸዋል። ከእርጥበት አዘል የአየር ሁኔታው ጋር ተያይዞም የተሻለ የዝናብ ስርጭት እንደሚኖር ገልጿል። በዚህም በደቡብ፣ በምዕራብ፣ በደቡብ ምዕራብ፣ በደቡብ ምስራቅ፣ በምስራቅ እንዲሁም በስምጥ ሸለቆ አካባቢዎች የተሻለ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚኖር አመልክቷል። በሚቀጥሉት ቀናት ከሚኖሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በመነሳት፤ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎችን ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ብዙ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ ብሏል። አልፎ አልፎ በውኃ አካላትና በአካባቢ አየር ውስጥ ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በመነሳት፤ በጥቂት የደቡብ፣ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች መጠቆማቸውን ገልጿል። ይህም ለግብርና ሥራ በቂ የአፈር ውስጥ እርጥበት እንዲኖር በማድረግ ለሰብሎች፣ ለግጦሽ ሳርና ለመጠጥ ውኃ አቅርቦት አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዳለው አስታውቋል። ከተፈጥሮና ሰው ሠራሽ የውኃ ማጠራቀሚያዎችን አቅም ለማሳደግ እንዲሁም ለቋሚ ተክሎችም አዎንታዊ ሚና እንዳለው ገልጿል። በተጨማሪም ለመኸር ሰብሎች የማሳ ዝግጅትና ዘር ለመዝራት፣ ፍሬ በማፍራትና በተለያየ የእድገት ደረጃ ላይ ለሚገኙ የበልግ ሰብሎች የውኃ ፍላጎት መሟላት፣ ለአረንጓዴ ዕፅዋት ልምላሜ፣ ለመጠጥ ውኃና ለግጦሽ ሳር አቅርቦት መሻሻል የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ተጠቁሟል። በተፋሰሶች ላይ ያለውን የእርጥበት ሁኔታ በተመለከተም ባሮ አኮቦ፣ መካከለኛና ታችኛው አባይ፣ በአብዛኛው ኦሞ ጊቤ፣ በላይኛውና መካከለኛው ስምጥ ሸለቆ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ የገጸ ምድር ውኃ ፍሰት ይኖራቸዋል ብሏል። በላይኛው ገናሌ ዳዋ፣ ኦጋዴን፣ ታችኛው ተከዜ እንዲሁም በላይኛውና መካከለኛው ዋቤ ሸበሌ ደግሞ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገጸ ምድር ውኃ ፍሰት እንደሚያገኙ ይጠበቃል ብሏል። በተጨማሪም ደረቅ የገጸ ምድር ውኃ ፍሰት የሚኖራቸው በአብዛኛው አፋር ደናኪል፣ አይሻ፣ መካከለኛና ታችኛው አዋሽ እንዲሁም በታችኛው ገናሌ ዳዋ መሆኑን የትንበያ መረጃዎች ያመላክታሉ ሲል ገልጿል። በሌላ በኩል በበልግ ወቅት የሚኖረው የሙቀት መጠን መጨመርና በሌሊት ደግሞ የሚታየው ወበቅ አንዱ የዚህ ወቅት ክስተት መሆኑን ጠቁሟል። ከሚኖረው ከፍተኛ የፀሐይ ኃይል ጋር ተያይዞም በተለይም በጋምቤላ፣ በአፋር፣ በሶማሌ፣ በቤንሻንጉል-ጉሙዝና በምዕራብ አማራ አካባቢዎች ላይ የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት ከ32 እስከ 41 ዲግሪ ሴልሺየስ እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል።
በክልሉ ከ261 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ ችግኞችን ለመትከል የ ጉድጓድ ቁፋሮ ስራ ተጀምሯል
May 20, 2026 1094
ባህርዳር ፤ግንቦት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከ261 ሺህ ሔክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ ችግኞችን ለመትከል የጉድጓድ ቁፋሮ ስራ መጀመሩን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር እስመለዓለም ምህረት ለኢዜአ እንደገለፁት የክልሉን የደን ሽፋን ቀድሞ ወደ ነበረበት ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ ነው። በመጭው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ የዋንዛ፣ ወይራ ፣ ዝግባ ፣ ፅድ ፣ አኬሺያ ዲከረንስ፣ ባህር ዛፍ፣ የፍራፍሬና ሌሎች ችግኞችን ለመትከል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የችግኝ ተከላውን በስኬት ለማከናወን እስካሁን 401 ሚሊዮን በላይ ጉድጓዶችን በማስቆፈር ለተከላ ዝግጁ ማድረግ መቻሉን አረጋግጠዋል። በቀጣይም የአረንጓዴ አሻራ ግብን ለማሳካት ተጨማሪ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶችን የማስቆፈር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። ባጠቃላይ በክረምቱ ለሚካሄደው ችግኝ ተከላ 261 ሺህ 297 ሄክታር መሬት ከወዲሁ ተለይቶ የጉድጓድ መቆፈር ስራው እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን የሰከላ ወረዳ አርሶ አደር መኮነን ልንገር እንደገለጹት ፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር መጀመሩ ተራቁተው የነበሩ አካባቢዎችን መልሰው በደን እንዲሸፈኑ ለማድረግ አስችሏል። መርሃ ግብሩ ለመኖ ፣ በንብ ማነብና እንስሳት እርባታ እያስገኝ ያለውን ተጠቃሚነት ለማስፋት በመጭው ክረምት በሚካሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በግልና በወል ቦታዎች ችግኝ ለመትከል ጉድጓዶችን እያዘጋጀን ነው ብለዋል። የሚተከሉት ችግኞች አያስገኙ ያለውን ጠቀሜታ በመረዳት በየዓመቱ ችግኞችን እያለማሁ ነው ያሉት ደግሞ በደቡብ ጎንደር ዞን የደራ ወረዳ አርሶ አደር ካሴ መንግስት ናቸው። በመጭው ክረምት የሚተከሉ ችግኞች ተንከባክበን በማሳደግ ለውጤት ለማብቃት ከወዲሁ ዝግጅት ጀምረናል ነው ያሉት። ባለፈው ክረምት በነቃ የህዝብ ተሳትፎ ከተተከለው ከአንድ ነጥብ አራት ቢሊዮን በላይ ችግኞች ውስጥ 80 በመቶ የሚሆነው መጽደቁን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በአፍሪካ የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ለመከላከል ሀገራት ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል
May 19, 2026 1141
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በአፍሪካ የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ለመከላከል ሀገራት ቅንጅታዊ አሰራራቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ፀባይ ትንበያ ማዕከል ጋር በመተባበር ለሁለት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየውን 73ኛውን የምስራቅ አፍሪካ የአየር ፀባይ አዝማሚያ ትንተናና ትንበያ ፎረም ተጠናቋል። በፎረሙ የቀጣናው ሀገራት ተወካዮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አጋር ድርጅት ተወካዮች እና ሌሎች አካላት ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርና በዓለም ሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፕሬዚዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ባለፉት ሁለት ቀናት በአፍሪካ ቀንድ ዙርያ ያሉ የኢጋድ አባል ሀገራት ያለፈው የበልግና መጪው ክረምት ወቅት የሚጠበቀውን የአየር ጠባይ ትንበያን አስመልክቶ ተወያይተዋል። በዚህም ሁሉም ሀገራት ከራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ በመነሳት የራሳቸውን የሜቲዎሮሎጂ መረጃዎችንና ከአካባቢያቸው አየር ሁኔታ በማገናዘብ ትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቅያ የሚሰጡበት ሁኔታ ላይ መነጋገራቸው አንስተዋል። ከአየር ትንበያው በመነሳትም የሚኖረው የአየር ሁኔታ በግብርና፣በውሃ፣በጤና ላይ ሊያደርሰ የሚችለው አሉታዊና አዎንታዊ ተፅእኖ በመገምገም ለቀጣይ ዝግጅት የሚደረግበት መሆኑ ተናግረዋል። እንዲሁም በህይወትና በንብረት ላይ ሊደርስ የሚችለውን የአደጋ ተጋላጭነትን ከመቀነስ አንፃር ጉልህ ድርሻ ያለው በመሆኑ መሰል መድረክ መዘጋጀቱ ጠቀሜታው የላቀ ነው ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚያጋጥሙ አደጋዎች በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ አደጋ እያደረሰ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ይህን ለመከላከል ሀገራት በቅንጅት መስራት አለባቸው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የአየር ንብረት ትንበያ እና የመተግበሪያ ማዕከል(ICPAC) ዋና ዳይሬክተር አብዲ ፊዳር (ዶ/ር) በአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የኢጋድ አባላት ሀገራት መረጃን መሰረት ያደረገ መረጃ በመለዋወጥ በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳሰበዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 2660
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 1517
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 1437
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በአዲስ አበባ ይካሄዳል
May 13, 2026 1481
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት በሕብረቱ ዋና መቀመጫ ዛሬ በአዲስ አበባ ይደረጋል። በውይይቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እንደሚገኙ ይጠበቃል። ውይይቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል በአፍሪካ ልማት እና በዓለም አቀፍ አስተዳደር ዙሪያ ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ቅንጅት፣ የጋራ ተጠያቂነት እና ትብብርን በልማት፣ በአስተዳደር፣ በሰብአዊ ድጋፍ እና በሰላም ግንባታ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ያላቸውን ትስስር ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ይካሄዳል። በዚህ የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ላይ በርካታ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች የሚዳሰሱ ሲሆን፣ በተለይም የአጀንዳ 2063 እና የሁለተኛው የአስር ዓመት ምዕራፍ የትግበራ ዕቅድ አፈፃፀምን ማፋጠን እንዲሁም አፍሪካን በዓለም አቀፍ ፖሊሲ እና አስተዳደር ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና መጠበቅ በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ትኩረት ያደርጋል። በተጨማሪም "ከጥገኝነት ወደ ሉዓላዊነት" የተሸጋገረ የልማት ፋይናንስ፣ የ2026 የአፍሪካ ሕብረት የዓመቱ መሪ ቃል የሆነው ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና የንጽህና አጠባበቅ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ተቋማት ሪፎርም እና አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ያላትን ውክልና የተመለከቱ ጉዳዮች ውይይት ይደረግባቸዋል። መድረኩ ለአህጉራዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔዎችን ማምጣት፣ የአገር ውስጥ ሀብት ማሰባሰብን ማሳደግ፣ የወጣቶች እና የሴቶች ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንዲሁም በአህጉራዊ እና በዓለም አቀፍ የልማት የቅድሚያ ትኩረቶች መካከል ያለውን ትስስር ማጠናከር ወሳኝ መሆኑ አጽንኦት የሚሰጥበት እንደሆነ ተመላክቷል። ከውይይቱ ከሚጠበቁ ውጤቶች መካከል የተሻለ ስትራቴጂካዊ ቅንጅት፣ ፍትሐዊ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ለውጥ፣ በአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ቃል ዙሪያ ጠንካራ ቅንጅት መፍጠር እና በተባበሩት መንግሥታት ሥርዓት ውስጥ ፍትሐዊ የአፍሪካ ውክልና እንዲኖር የቀረቡ ጥሪዎችን ማጠናከር እንደሚገኙበት ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የውይይቱን ውጤቶች አስመልክቶ የጋራ መግለጫ ይሰጣሉ።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 24, 2026 371
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የመደመር ማሳያ ከሳምንቱ አበይት ክስተቶች መካከል የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች በአሶሳ ከተማ ያስገነቡት የጋራ ሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህንፃ ምረቃ ይጠቀሳል። በክልሎቹ ትብብር የተከናወነው የህንፃ ግንባታ በመደመር እሳቤ የዜጎችን የጋራ ሰላም ለማስጠበቅና የልማት ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ ጥረት ማሳያ ነው። መርሃ ግብሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) የተገኙበት ነበር። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም ላይ ያተኮረው መድረክ በሶማሌ ክልል ጂግጂጋ ከተማ የተካሄደውና በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ ያተኮረው ፎረምም በእዚህ ሳምንት ዐበይት ጉዳይ ነበር። ፎረሙ የተካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን የተዘጋጀውም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ጠቅሰዋል። እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልጽነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑም በቀጣናው ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ ነው ያነሱት። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ምሁራን ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ እንዲያስቀምጡም ያግዛል ብለዋል። የጉባ ላይ ብስራቶች ተግባራዊ ልማት የሳምንቱ የበረራ ቅኝታችን የሚጀምረው ወደ ሶማሌ ክልል ጎዴ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በስፍራው እየተገነባ ያለውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላም በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት የመሬት፣ ውሃ እና የሚያለማ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በቂ ሃብት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህን ካሟላን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ማድረግ ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የኒውክለር ሃይል ማመንጫ፣ የቢሾፍቱ አየር መንገድ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የቤቶች ልማት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጓቸው የጉባ ብስራቶች መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀው ስራ ያስጀምሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በግራንዴር ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተገነባው ፋብሪካ፣ መሰረት ልማቱ በ300 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ፣ የዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የሴራሚክና የፎርሲሌን ንጣፎች ማምረቻ ፋብሪካ ነው። የፋብሪካው መገንባት የውጭ ምርት ጥገኝነት ከመቀነስ ባለፈ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑ ታውቋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ ጉብኝት በዚሁ ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ወደ ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጓዝ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በድሬዳዋ ቆይታቸው ብርቱካንና ሌሎች የፍራፍሬ ልማት ሥራዎች እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ልማት ስራን ተመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የግብርና ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባስተላለፉት መልእክትም የጋራ ሙለታ ተፈጥሯዊ የልማት ፀጋና ከፍታም ታሪክን፣ ውብ መልክዓ ተፈጥሮን የታደለ፣ የኢትዮጵያን ሜዳና ተራሮች ምርት የሚታፈስባቸው የማድረግ ሀገራዊ ጉዞ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ማሳያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ ተገኝተው 142 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ ያስጀመሩትም በዚህ ሳምንት ነበር። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በለውጡ ዓመታት ከልማት የራቁ አካባቢዎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ መሰራቱን አንስተዋል። የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የንጽህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶች ለዚሁ ማሳያ ናቸው ብለዋል። በተመሳሳይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ እና የመስኖ ፕሮጀክቶች መርቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በተለይ አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልት የሚያስቀር ነው። የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። በሲዳማ ክልልም በፌደራል መንግስት ድጋፍ በ460 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታም ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 75 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ነው። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከ543 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 52 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መመረቃቸው ሌላው የሳምንቱ ክስተት ነበር። በዞኑ ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትንም መርቀዋል። ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግበት የሃዋሳ ከተማ ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም በዚህ ሳምንት ተካሂዳል። ለፕሮጀክቱ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ የፕሮጀክቱ ግንበታ ሲጠናቀቀ ሀዋሳ ከተማዋን ጽዱ በማድረግ የቱሪዝምና የኢንቨስመንት ማዕከልነቷን ያሳድገዋል ተብሏል። አቶ ደስታ የፕሮጀክቱ ግንባታ መንግስት ለከተሞች እድገት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉም ነው የጠቀሱት። የከሰም መስኖ ግድብ የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክትም በዚሁ ሳምንት ተመርቆ ሥራ ጀመሯል። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ነው። የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ያስቀራል ተብሏል። በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብርሃም (ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር። የጥገና ማሻሻያው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን ይህን የአደጋ ስጋት በማስቀረት ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል የሚያስችል ነው። ለፕሮጀክቱም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ሚኒስትሩ አንስተዋል። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል። የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የሀዝቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም አንስተዋል። የግንቦት - ታላቁ ሁነት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ሂደቱን ስኬታማ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አጠቃላይ ዜጎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በዚሁ ሳምንት "ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የመገናኛ ብዙሃን ሚ ና" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአዳማ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎና የዳበረ የዴሞክራሲ ልምምድ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅም መገናኛ ብዙሃን የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ከተረጅነት የመውጣት ሀገራዊ ጥረት በድሬዳዋ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረክም ሌላው የእዚህ ሳምንት ዓቢይ ጉዳይ ነው። መድረኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የግብርና ሚኒስቴር በመተባበር ያዘጋጁት ነው። በመድረኩም በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተነስቷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቂና የተሟላ የውሃ ሀብት፣ የተማረና አምራች የሆነ ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም ለም የመሬት ፀጋዎች ያሉባት ሀገር በመሆኗ በማልማት እድገትና ማንሳራራትን ማስቀጠል ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። ለእዚህም ዋናው መሠረታዊ ጉዳይም ያሉ አቅሞችን በመለየትና ህዝብን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ በማሸጋገር በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጡን ሥራ በላቀ ደረጃ ማስቀጠል መቻል መሆኑን አንስተዋል። ለሰላም ጥሪ የተሰጠ ምላሽ የሠላም ጥሪን የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም (ዲዲአር) መርሀግብርም በዚህ ሳምንት ተከናውኗል። በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል ጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ ሆነው የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ታጣቂዎቹ ሠላምን አማራጭ በማድረግና የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፣ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል። በተመሳሳይ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የክልሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮምቦልቻ የስልጠና ማዕከል ስልጠና የጀመሩ መሆኑ ይታወቃል። ሐረር- ፕሮጀክቶች ምረቃ የሐረሪ ክለል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙትን የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝትም ሌላው የእዚህ ሳምንት ኩነት ነበር። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተሻለ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ። በተለይም የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መገንባት የክልሉን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የበለጠ በማሳደግ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት። በዘመናዊ ትምህርት የታነፀና በእውቀት የበለፀገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማፍራት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቶቹ በፍጥነትና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ለማስቻል በአስተዳደሩ በኩል ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት 672 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በይፋ የተመረቀውም በዚህ ሳምንት ነው። በምረቃው ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን፣ የክልሉ የመንገዶች ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢድሪስ ሙሴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እንደገለጹት ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የከተማውን የንግድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያስችል ነው። የከተማውን ገፅታ በመለወጥ ረገድም የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ነው ያነሱት። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገድ ፕሮጀክቱ የጂግጂጋ ከተማን ልማትና ዕድገት በማፋጠን በኩል ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን አስተዳደሩ ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ዕቅድን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 30 ሜትር ስፋት እንዳለውም ታውቋል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 1817
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 2052
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 1874
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት
May 24, 2026 1320
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኝ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአንጀት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች በውል ይታወቃሉ? ቀድሞስ መከላከል ይቻላል? የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። ለምን ቢሉ? ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ስላለው ይሆናል መልሱ። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫዎት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁንእንጅ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል።ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚህ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዐለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዐለም ዐቀፍ፣ አኅጉር ዐቀፍ እና ሀገር ዐቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ይህም ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫዎታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል። #የኮሪደር_ልማት #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 579
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት
May 17, 2026 4102
በኢዜአ ዐይን …! በዮሐንስ ደርበው እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለእንግልትና ብልሹ አሠራር አጋላጭ ሁኔታዎች ይስተካከሉን የሚሉ እሮሮዎች በተለያዩ ሕዝባዊ ውይይቶች ሲነሱ ቆይተዋል። በተለይም በአንዳንድ ተቋማት መንግሥታዊ አገልግሎት ለማግኘት እዚያም እዚህም መንከራተት፤ደግሞም ወረፋ በመጠበቅ መጉላላት ብሎም ለጊዜና ገንዘብ ወጪ መዳረግ ይስተዋላል የሚሉ ሐሳቦች ተስተጋብተዋል። ሾተላይ ምንድነው? እንዴትስ ይከሰታል? ቀድሞ መከላከልስ ይቻላል? ባሳለፍነው ሳምንት … መንግሥትም የተነሱ ቅሬታዎችን ማረቅ የሚያስችል አሠራር በመንደፍ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ ብሎ አስጀመረ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማዕከሉ አገልግሎት ባስጀመሩበት ወቅትም ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሠራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው ብለው ነበር። አሁን ላይም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋ ነው።መስፋፋቱም በማዕከላት ብዛት፣በአገልግሎት መስጫ መስኮቶች ቁጥር እና በአገልግሎት ዐይነቶች እየተገለጠ ነው። በዚህም በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት የተደራጁ ሲሆን ይህ አሃዝም ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት እና ያለውን ፈጣን እድገት ያመላክታል። ጉዳዩ የዜጎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ማላቅ፤ ብልሹ አሠራርንም መቅረፍ ነውና መንግሥት በልዩ ትኩረት ይዞታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ አሥተዳደርና በሐረሪ ክልል ጉብኝት ባደረጉበት ወቅትም፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የምልከታቸው አካል ማድረጋቸው ለጉዳዩ የተሰጠውን ከፍያለ ትኩረት ያሳያል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሶብ የሞባይል አገልግሎትን በመረቁበት ወቅት ደግሞ፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ብለዋል። አክለውም፤በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች ዕርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል፤ ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፤ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ መሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል ማለቱም ይታወቃል። የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አንተነህ ማሞ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ደግሞ፤ ዘመናዊና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር የተገልጋዮችን እርካታ ማረጋገጥ ያስቻለ ስኬት ተገኝቷል ብለዋል። በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጡ የመንግሥት አገልግሎቶችም ዜጋ ተኮር፣ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍልና የተገልጋዮችን ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ መሆናቸውን አብራርተዋል። በዲጂታል 2030 የአገልግሎት አሰጣጥ አመላካች ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚጠቀሱ 50 ሀገራት መካከል አንዷ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል። ዜጎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በኦንላይን በየትኛውም ቦታ ሁሉንም አገልግሎቶች እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ ስለመሆኑም እንዲሁ። አገልገሎቱን ያገኙ አስተያየት ሰጭዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ እንግልትን ያስቀረ፣ ጊዜና ወጭን የቀነሰ ነውና ይስፋፋ፤ ተጠናክሮም ይቀጥል። #መሶብ_የአንድ_ማዕከል_አገልግሎት #የዜጎችን_እንግልትና_ብልሹአሠራርን_መቅረፍ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #በኢዜአ_ዐይን
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 17, 2026 2149
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 2 እስከ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ጋር መምከራቸው ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም በኢኮኖሚያዊ እድገት፣ በአጋርነት እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል። ለነበረን ጠቃሚ የሐሳብ ልውውጥና ቀጣይነት ላለው አጋርነትም ምስጋናዬ የላቀ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። · ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ በኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና በፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በጋራ አዘጋጅነት በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባዔ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ተሞክሮ አካፍለዋል። በዚሁ ወቅትም በተለይም የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት እና የኃይል ሽግግርን በተመለከተው ውይይት ላይ ከተሞክሯችን የተቀዱ ከፍ ያሉ ሐሳቦች ተነስተዋል ብለዋል። አክለውም፤ ኢትዮጵያ በተነሱት ሁለት ዘርፎች የጀመረችውን ሥራ በማጠናከር የላቀ ሚና መጫወቷን ትቀጥላለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንኳን ደህና መጡ ስል ሁልጊዜም በልዩ ኩራትና ደስታ ነው ሲሉ ተቀብለዋቸዋል። ከአቀባበሉ በኋላም፤ መሪዎች በጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በዚህም መሠረት፤ በታዳሽ፣ የተቀናጀ እና ዘላቂ ኃይል እንዲሁም የዲጂታላይዜሽን ፕሮግራምን ለመተግበር የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊየን ዩሮ ብድርን ጨምሮ የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል የመንግሥትና የግል አጋርነት አዲስ የማዕቀፍ እና የፍኖተ ካርታ ስምምነት ተፈርሟል። · ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የስምንት አስርት ዓመታት ጉዞን ምክንያት በማድረግ፣ "በሰላም አብሮ ለመኖር" በሚል መሪ ቃል ልዩ የመታሰቢያ ቴምብር ስብስብ ማውጣቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርገዋል። እነዚህ አራት ቴምብሮች እ.ኤ.አ. በ1945 በሳን ፍራንሲስኮ የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን ከመፈረም ጀምሮ፤ በኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይሎችን እስከማሰማራት እና በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደውን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ እስከ ማስተናገድ ያለውን የጋራ ታሪካችንን የሚተርኩ ናቸው ብለዋል። በዓለም የፖስታ ኅብረት በኩል ለ192 ሀገራት የተሰራጩት እነዚህ ቴምብሮች፤ ለአንድ ወቅት ብቻ ሳይሆን ለትውልድ ሁሉ የሚተርፍ የታሪክ ዐሻራ ማሳያ መሆናቸውንም አስታውቀዋል። በተያያያዘም፤ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ለቡድናቸው፣ በዘመናዊው ታሪክ ውስጥ እጅግ ፈታኝ በሆነ ወቅት ላይ ሰላምን፣ ልማትን እና ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እያሳዩት ላለው ጽኑ አመራር ጥልቅ አድናቆታችንን እንገልጻለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የተባበሩት መንግሥታት የጸናው ሀገራት ከመከፋፈል ይልቅ ውይይትን ስለመረጡ መሆኑን አስገንዝበው፤ ኢትዮጵያም ይህንኑ የሁልጊዜ ምርጫዋን ታጸናለች ሲሉ አረጋግጠዋል። · የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅትም የምክክር ባህል እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበው፤ ጠንካራ የሲቪክ ማኅበረሰብ ባህል ግንባታ ደግሞ ያላሰለሰ የመነጋገር ልምምድ እና የሰከነ የወል መደማመጥን ግድ ይላል ብለዋል። የእስካሁን ሂደቱም በማኅበረሰባችን በየደረጃው የመደማመጥን ከፍ ያለ ጠቀሜታ አሳይቷል ሲሉም ገልጸዋል። ሂደቱ በሀገራችን ሁሉም ማዕዘናት የሚገኙ ከ90 በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያንን አመለካከቶች እና የውይይት ውጤቶች ያንፀባረቀ ሆኗልም ነው ያሉት። ለሀገር ወሳኝ ፋይዳ የያዘው የምክክሩ ምዕራፍ ተጨባጭ ውጤት ወደሚያስገኘው ቀጣይ ምዕራፍ በሚሸጋገርበት በዚህ ወቅት፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለሀገራችን ሰላም፣ አንድነት እና ዘላቂ መረጋጋትን የሚያረጋግጥ የጋራ ፅኑ አቋም እና ገንቢ በሆነ መንገድ አስተዋፅኦ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል። · የገላን ኢንዱስትሪ ፓርክ መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን በመረቁበት ወቅት፤ ፓርኩ አስተማማኝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት በጀመርነው የብልጽግና ጉዞ ተደማሪ እመርታ ነው ብለዋል። ለመካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች ምቹ የንግድ ከባቢ ከመፍጠር ባሻገር በሺዎች ለሚቆጠሩ ወጣቶቻችን የሥራ ዕድል ይከፍታል ሲሉም ገልፀዋል። ፓርኩ የሀገራችን አምራቾች አቅማቸውን በማጎልበት፣ ምርታማነታቸውን ማሳደግና ተወዳዳሪነታቸውን በመጨመር ለከተማችን፣ ለሀገራችንና ለቀጣናው የሚተርፉበት ታላቅ እድልን ይዟል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተኪ ምርቶችን በማምረት በአምራቾችና በሸማቾች መካከል ቀጥተኛና ቀልጣፋ የንግድ ትስስር ይፈጥራል፤ ምርቶችን ደግሞ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የሀገራችንን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይጫወታል ሲሉ አስረድተዋል። · ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔ መጀመር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት ዓለም አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት ጉባዔን ባስጀመሩበት ወቅት፤ ኢትዮጵያ ለልማት በምታደርገው ቆራጥ ጥረት ውስጥ የሰው ተኮር የልማት አቅጣጫ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት መንግሥት መጪው ትውልድ ጤናማ፣ ብቁ እና ውጤታማ እንዲሆን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ማዕከል በማድረግ ሁሉን አቀፍ ሥራ እየተገበረ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በመላ ሀገሪቱ ከ35 ሺህ በላይ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት የነጻና አስገዳጅ ትምህርት ተደራሽ እንዲሆን እያደረግን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ልጆች ላይ መሥራት በነገ ሀገር ላይ መሥራት በመሆኑ ተባብረን፣ በጊዜ የለንም መንፈስና በትጋት እንሥራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። · የፖሊሲ ቀን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ ባሳላፍነው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው የፖሊሲ ቀን ተከብሯል። በዚሁ ወቅትም፤ ውጤታማ ፖሊሲ ለሀገራዊ ዕድገት የጀርባ አጥንት መሆኑን አስገንዝበው፤ መንግሥት በግልፅ፣ ተተግባሪና ጥራት ባላቸው ፖሊሲዎቹ ለሕዝብ የገባውን ቃል እየተገበረ ስኬትም እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ሀገራችን ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በምትገኝበት በዚህ ወቅት ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ በጂኦ-ፖለቲካዊና በቴክኖሎጂ ለውጦች ላይ ቀድሞ ምላሽ የሚሰጡ ጥናቶች ያስፈልጋሉ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በዕውቀት ላይ ኢንቨስት በማድረግ እና ለማስረጃዎች ዋጋ በመስጠት፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ የፖሊሲ ሥነ-ምኅዳር ለመገንባት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ለዚህ ስኬት ሁላችንም በጋራ እንሥራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 7483
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 4494
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 10281
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 8757
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 2149
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 2567
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው። በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል። የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል። ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።