ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታዎች
Feb 24, 2026 50
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ ዛሬ አራት የመልስ ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ማንችስተር ዩናይትድ ኤቨርተንን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ አራተኛ ከፍ አደረገ ምሽት አምስት ሠዓት ላይ ኢንተር ሚላን ከቦዶ ግሊምት በሳን ሲሮ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ቦዶ ግሊምት 3 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ኢንተር ሚላን ወደ ጥሎ ማለፍ ለመግባት ከሁለት ጎል በላይ ልዩነት ማሸነፍ ይኖርበታል። ተጋጣሚው ቦዶ ግሊምት ማሸነፍ፣ አቻ መውጣት እና በአንድ የግብ ልዩነት መሸነፍ 16ቱን መቀላቀል ያስችለዋል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ኒውካስትል ዩናይትድ ከካራባግ ምሽት አምስት ሠዓት ላይ በሴይንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በመጀመሪያው ጨዋታ 6 ለ 1 ያሸነፈው ኒውካስትል ዩናይትድ የማለፍ እድሉ እጅጉን ሰፊ ነው። በአንጻሩ ተጋጣሚው ካራባግ በሂሳባዊ ስሌት ወደ ጥሎ ማለፍ የመግባት እድሉ በጣም የጠበበ ነው። ባየር ሌቨርኩሰን ከኦሎምፒያኮስ ምሽት አምስት ሠዓት ላይ በቤይአሬና ስታዲየም ይጫወታሉ። የጀርመኑ ባየር ሌቨርኩሰን በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ከሜዳው ውጪ 2 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ውጤቱንም ተከትሎ የማለፍ እድሉን አስፍቷል። የግሪኩ ኦሎምፒያኮስ ወደ ጥሎ ማለፍ ለመግባት ከሁለት ጎል በላይ ልዩነት ማሸነፍ አለበት። ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ አትሌቲኮ ማድሪድ ከክለብ ብሩዥ በዋንዳ ሜትሮፖሊታኖ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሁለቱ ክለቦች ባለፈው ሳምንት ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ ሶስት አቻ ተለያይተዋል። የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፈው ቡድን ጥሎ ማለፍ ይገባል።
ማንችስተር ዩናይትድ ኤቨርተንን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ አራተኛ ከፍ አደረገ
Feb 24, 2026 77
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/ 2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሐ-ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በሂል ዲኪንሰን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ተቀይሮ የገባው ቤንጃሚን ሼሽኮ በ71ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በጨዋታው ላይ ኤቨርተን የተሻሉ የግብ እድሎችን ቢፈጥርም የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የነበረው ማንችስተር ዩናይትድ ያገኘውን አጋጣሚ ወደ ግብ በመቀየር አሸናፊ ሆኗል። የዩናይትዱ ግብ ጠባቂ ሴን ላመንስ የጨዋታው ኮከብ ተጫዋች ሆኖ ተመርጧል። በሊጉ 13ኛ ድሉን ያስመዘገበው ማንችስተር ዩናይትድ በ48 ነጥብ ደረጃውን ከአምስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለመሳተፍ በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። እንግሊዛዊው ጊዜያዊ አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ በሊጉ አምስተኛ ድሉን አሳክቷል። ቡድኑ በካሪክ ስር እስከ አሁን አልተሸነፈም። በአንጻሩ በሊጉ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኤቨርተን በ37 ነጥብ 9ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል።
የጽንፈኛው ሃይል አመራሮችና አባላት የሰላም ጥሪውን ተቀብለው መግባት ቀጥለዋል
Feb 23, 2026 118
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የጽንፈኛው ሃይል አመራሮችና አባላት መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ በመቀበል መግባት መቀጠላቸውን በመከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ አስታወቀ። እዙ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው የሰላምን አማራጭ የተቀበሉት የቡድኑ አመራሮችና አባላት በጎጃም ቀጣና የሚንቀሳቀሱ ናቸው። ለጥምር ጦሩ እጅ የሰጡት የጽንፈኛው ቡድን አመራሮችና አባላት መርዓዊ ከተማ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የቡድኑ አመራሮችና አባላት የገቡት 1 ፒ ኬ ኤም/መትረየስ ፣ 11 ክላሽ፣ 2 ኤስኬስ፣ 2 ፋል፣ 4 ቦንብ፣ 1 የመገናኛ ሬዲዮን ጨምሮ የተለያየ መሳሪያ ጥይቶችንና ካዝናዎችን በመያዝ ነው። በሰላም ከገቡትና በተለያየ ደረጃ ላይ ከሚገኙት 22 አመራሮችና አባላት መካከል አስር አለቃ ቻላቸው አስናቀ(ቻቻ) ፣ ቢኒያም ጋሻው፤ ጋሻው መኳንንት ፣ዘላለም አዱኛ ፣እንዳላማው ገብሬ እና ጋሻ ታደለ የተባሉ አመራሮች እንደሚገኙበት ተገልጿል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወሳኝ ድል አሳክቷል 
Feb 23, 2026 61
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሸገር ከተማን 3 ለ 2 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ረድኤት አስረሳኸኝ ሁለት ግቦችን ስታስቆጥር እፀገነት ግርማ ቀሪዋን ጎል ለንግድ ባንክ ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ሰናይት ኡራጎ እና ገነሜ ወርቁ ለሸገር ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በውድድር ዓመቱ 11ኛ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ35 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። የወቅቱ የሊጉ ዋንጫ አሸናፊ ንግድ ባንክ ከሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ አድርጓል። በአንጻሩ በሊጉ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሸገር ከተማ በ27 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ዛሬ በተደረገ ሌላኛው መርሐ-ግብር ሃዋሳ ከተማ እና አዳማ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 14ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ15ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከየካቲት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳሉ።
የሚታይ
ዛሬ በዲፕሎማሲው መስክ እያየን ያለነው ስኬት ሁሉ፣ ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ያላትን የተገቢነት ቦታ ዳግም ያረጋገጠ ነው
Feb 23, 2026 100
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ዛሬ በዲፕሎማሲው መስክ እያየን ያለነው ስኬት ሁሉ፣ ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ያላትን የተገቢነት ቦታ ዳግም ያረጋገጠ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ንጋት ከድምጽ አሰሚነት ወደ ተሰሚነት! የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ መዝገብ ሲገለጥ የሚነበበው በክብር የቆመ የታሪክ መሠረት፣ ነገር ግን እንደ ጥንታዊነቷ ድምጿ ጎልቶ የማይሰማበት የቆየ አሠራር ነበር። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው ድል ግን ይሄንን የተገደበ ተሳትፎ በመስበር፣ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ መድረክ ዋነኛ ተዋናይ ያደረገ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።   የለውጡ መንግሥት ዲፕሎማሲን እንደ ሀገራዊ ሉዓላዊነት መጠበቂያ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ብልጽግና ምንጭ በመቁጠር በብርቱ ሠርቷል። ዛሬ የዚህ ብልህ ዲፕሎማሲያዊ ሥራ ፍሬ እያፈራ፣ የሰላም እና የትብብር ጥረቱ አዝመራ እየታጨደ ነው፡፡ ለዚህ ሥር ነቀል ለውጥና ኢትዮጵያን በጎረቤት ሀገራት እና በአህጉር ደረጃ ያላትን አቀራራቢ ሚና በማጠናከር፣ የቀጣናውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የነበረውን የቆየ እሳቤ መቀየር ተችሏል። ሀገርን ማዕከል ያደረገ፣ ክብሯን እና ጥቅሟን የሚያስከብር ተለዋዋጭ ዲፕሎማሲ በመከተል ለተገኘው ስኬት ደግሞ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ቁልፍ መሐንዲስ ናቸው። የኢትዮጵያ ወደ BRICS+ መቀላቀል፣ በአፍሪካ ኅብረት እና በተባበሩት መንግሥታት መድረኮች ላይ የሚቀነቀነው አቋሟ፣ እንዲሁም በዓለም አቀፍ መሪዎች ዘንድ ያገኘችው ከፍ ያለ ተቀባይነት የዚሁ የጠራ ራዕይ ውጤቶች ናቸው።   ዛሬ በዲፕሎማሲው መስክ እያየን ያለነው ስኬት ሁሉ፣ ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ያላትን የተገቢነት ቦታ ዳግም ያረጋገጠ ነው፡፡
በመዲናዋ የ97 ሺህ ቤቶች ግንባታ እየተፋጠነ ነው -ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Feb 23, 2026 95
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ለመገንባት ከታቀደው 100 ሺህ ቤቶች ውስጥ የ97 ሺህ ቤቶች ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝ የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ከተማ አስተዳደሩ እያካሄደ ካለው ዘርፈ ብዙ ልማት ውስጥ ለቤት ልማት ልዩ ትኩረት መስጠቱን አመልክተዋል።     በ2018 ዓ.ም ለማከናወን ከታቀደው 100 ሺህ የቤቶች ግንባታ ዉስጥ የ97 ሺህ ቤቶች ግንባታ በአስደናቂ ሁኔታ እየተፋጠነ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል። በግንባታ ላይ ካሉ 17 ሳይቶች መካከል በገርጂ፣ በቱሉ ዲምቱ፣ በገላን ጉራ (የመጀመሪያና ሁለተኛ ምዕራፍ)፣ በአቃቂ ቃሊቲ (ወርቁ ሰፈር) እንዲሁም በንፋስ ስልክ ላፍቶ የገበያ ማዕከል እየተገነቡ ያሉትን ቤቶች አፈጻጸም ዛሬ መገምገሙን ጠቁመዋል። ግምግማ የተደረገባቸው ሳይቶች ፕሮጀክቶች ከተጀመሩ ከ6 እስከ 7 ወር ቢሆንም፣ ቀን እና ማታ ያለማቋረጥ በመስራት ፤ እጅግ ትጉ በሆኑ ኢትዮጵያዊ ኮንትራክተሮች፣ ማህበራት፣ አማካሪዎች፣ ትጉ አመራሮች እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ በአሁኑ ወቅት አበረታች ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል። በሳይቶቹ ከ200 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩንና በርካታ ኮንትራክተሮችና ማህበራት በአዲስ የሥራ ተነሳሽነትና በትጋት እየተሰሩ ይገኛል ነው ያሉት። የከተማ አስተዳደሩ ትኩረት የቤቶቹ ግንባታ ፍጥነት ብቻ ላይ ሳይሆን፣ ከቤት አቅርቦት የዘለለ በተሻሻለ ዲዛይን ጤናማ፣ ውብና ዘመናዊ የመኖሪያ መንደሮችን መገንባት ላይ ነው ብለዋል።   የግንባታ ጥራት ለማረጋገጥ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአማካሪነት ከከተማ አስተዳደሩ ጋር እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። እየተገነቡ ካሉት ቤቶች ውስጥ 50 ሺዎቹ በከተማው በጀት የሚገነቡ ሲሆን የተቀሩት 50 ሺዎቹ ደግሞ የሚገነቡት በመንግስትና የግል አጋርነት መሆኑን ጠቁመዋል። ከለውጡ በፊት እንደዚህ አይነት ሰፊ የቤት ልማት አይደለም በከተማው በጀትና በአንድ አመት ቀርቶ በተለመደው የባንክ ብድር እንኳን በየአምስት አመቱ 100 ሺህ ተሰርቶ ቢሆን ኖሮ ዛሬ በሚሊዮኖች ተመዝግበው ለረጅም አመታት እስከ ዛሬ የሚጠባበቁ እና ከ60 ቢሊዮን በላይ የኮንዶሚንዬም የቦንድ እዳን ተረክበን ለመክፈል እና ለማስተናገድ ባልተገደደን ነበር ብለዋል። አሁን እየተገነባ ያለው ቤት ከነዋሪዎች ሰፊ ፍላጎት አንጻር አቅርቦቱ ገና ቢሆንም፣ የቤት ችግርን በዘላቂነት የመፍታት ስራችን ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ከንቲባዋ በመልዕክታቸው ላይ ያሰፈሩት።
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ትንበያ ካሉ ተጨባጭ ውጤቶች የመነጨ ነው - የዘርፉ ምሁራን
Feb 23, 2026 95
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ትንበያ በመሬት ላይ ካሉ ተጨባጭ የልማት ሥራዎችና ስኬቶች የመነጨ መሆኑን የኢኮኖሚ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት፤ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ የ10 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት እንደሚያስመዘግብ መግለጻቸው ይታወሳል። መንግሥት የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ በወሰዳቸው እርምጃዎች የዋጋ ንረትን ወደ ነጠላ አሃዝ በማውረድ ትልቅ ስኬት መመዝገቡንም አመልክተዋል፡፡ በዚህም የዋጋ ንረትን ወደ 9 ነጥብ 7 በመቶ ነጠላ አሃዝ በማውረድ ከፍተኛ ስኬት መመዝገቡን ጠቅሰው፥ አሁንም ብዙ መስራት ይጠበቃል ብለዋል። የኢኮኖሚ ምሁሩ ደረጄ ደጀኔ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ መንግሥት ተግባራዊ ያደረገው አጠቃላይ የኢኮኖሚ ሪፎርም ለታየው ተከታታይ ዕድገት መሠረት ሆኗል። በተለይም በግብርና ዘርፍ ባለፉት ስድስት ዓመታት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት በሆነው በዚህ ዘርፍ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል ብለዋል። በኢንዱስትሪው ዘርፍ "ኢትዮጵያ ታምርት" በተሰኘው ብሔራዊ ንቅናቄ የሀገር ውስጥ አምራቾች አቅም እንዲጠናከርና የገቢ ምርቶች በሀገር ውስጥ እንዲተኩ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየታዩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በማዕድን ልማት ዘርፉ ሌላው አስደናቂ ውጤት እየተመዘገበበት ያለ የኢኮኖሚ ምንጭ መሆኑን ጠቁመው የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት የሀገሪቱን ዕድገት እያረጋገጡ መሆናቸው የዘንድሮው የ10 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ትንበያ ስኬታማ እንደሚሆን ማሳያ ነው ብለዋል።   የኢኮኖሚ ምሁር ጀማል መሐመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ቀውስ ባለበት ወቅት ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለው ዕድገት ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል። ይህ ዕድገት ለወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ አዳዲስ የኢንቨስትመንት መስኮችን ለማስፋፋት እና ሌሎች ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን እንደሚያግዝ አስታውቀዋል። የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ውጤት እያመጡ መሆኑንና ግሽበቱን ወደ ነጠላ አሃዝ ዝቅ ማድረግ መቻሉ አስደናቂ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥት የኤክስፖርት ገቢን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ መቻሉ የሀገሪቱን የዕዳ ጫና ለመቀነስ ትልቅ ሚና እንደተጫወተ ምሁራኑ አስረድተዋል። ይህም በቀጣይ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጨማሪ የፋይናንስ አቅም እንደሚፈጥር አመልክተዋል። አሁን እየተወሰዱ ያሉ የፖሊሲ እርምጃዎች ተጠናክረው ከቀጠሉ፣ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዓመታት የላቀ የብልጽግና ደረጃ ላይ እንደምትደርስ ምሁራኑ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።    
የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ ዓላማ ትናንትን በማከም ነገን የተሻለ ማድረግ  ነው - ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)
Feb 23, 2026 132
ቦንጋ፤ የካቲት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ ዓላማ ትናንትን በማከም ነገን የተሻለ ማድረግ ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ምልክቱን(የስንዴ ነዶ) እና ማኒፌስቶ የማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በቦንጋ ከተማ አካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለፁት የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ አላማ በሀገረ መንግስቱ ግንባታ ሂደት ውስጥ ያጋጠመውንና ትናንትን በማከም ነገን የተሻለ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል።   በኢኮኖሚው ዘርፍ ያጋጠመውን የተዛባ መዋቅራዊ ችግር በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ለመፍታት ፓርቲው ባደረገው ጥረት ባለፉት ዓመታት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ለአብነት አንስተዋል። በዚህም በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት በአለም እውቅና የተሰጠውን ድል ማስመዝገቡን ጠቅሰው የዘመናት ቁጭት የነበረውን የህዳሴ ግድብ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት አብቅቷል ብለዋል። በክልሉም የግብርና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ፣ የገቢ አቅምን ለማሳደግ እንዲሁም በስራ ዕድል ፈጠራና በሌሎችም ዘርፎች በተደረጉ ሰፊ ርብርቦች በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡ በማህበራዊ ዘርፍም የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ተወዳዳሪና ብቁ ትውልድን መፍጠርና ጤናማ ትውልድን ለማፍራት የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ ናቸው ብለዋል፡፡ በዚህም የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር እንደሀገር የተያዘውን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ በክልሉ ያሉ አቅሞችን ለይቶ የማልማት ስራ በትኩረት እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡   በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፤ የብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉና ሀገርን የሚያሻግሩ ውጤቶች ማስመዝገቡን ገልጸዋል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልም ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተደረገው ርብርብ ፍሬ እያፈራ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም የህዝቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አንስተው በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ ድሎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር ለማድረግ መንገዱ ብልፅግና ነው ብለዋል። በመርሃ ግብሩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ውጤት እያመጡ ነው
Feb 23, 2026 84
አዳማ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የከተማና መሰረት ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለፁ። ሚኒስቴሩ የ2018 በጀት አመት የስድስት ወራት የሴክተር ስራዎች አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የክልሎች የዘርፉ አመራሮችና የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአዳማ ከተማ እያካሄደ ነው። ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በወቅቱ እንደገለፁት በለውጡ መንግስት ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው።   የከተማ ነዋሪዎች ህይወት ከመለወጥ፣ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ፣ የመሬት አስተዳደር ስርዓት ከማዘመንና የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ችግሮች ከማቃለል አኳያ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። የከተሞችን መሰረተ ልማት በማስፋፋትና ዲጂታል አገልግሎትን ተደራሽ ከማድረግ አንፃር ተስፋ ሰጪ ተግባራት መከናወናቸውንም አመልክተዋል። በተለይ የኮሪደር ልማት በከተሞች መሰረተ ልማት ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ገፅታቸውን በመቀየር በኩል ተጨባጭ ለውጦች የተገኘበት መሆኑን ተናግረዋል። በኮሪደር ልማቱ የመደመር መንግስት እሳቤዎች ውጤት የታየበትና የከተሞች የገፅታ ለውጥ ያየንበት ነው ሲሉም አክለዋል።   በዚህም ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን በጥራትና በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅም ባህል እየሆነ የመጣበት መሆኑን ጠቁመው ልማቱ የህዝብና የመንግስት ትብብር የታየበት እንደሆነም አንስተዋል። በከተሞች የተገልጋዩን ህብረተሰብ ዕርካታ ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመው የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንና ከተሞች ለኑሮና ለስራ ምቹ እንዲሆኑ ከማድረግ አኳያ ተስፋ ሰጪ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። አረንጓዴ ልማቱም የከተሞችን ውበት ከማስጠበቅ ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር እንደቻለም ሚኒስትሯ ጠቅሰዋል። በቀሪው ሁለተኛው ግማሸ በጀት ዓመት ዲጂታል አገልግሎትን ማስፋፋት፣ በተለያዩ ከተሞች እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ማጠናቀቅ፣ የውበትና አረንጓዴ ልማት ስራዎችን ማጠናከር፣ የመኖሪያ ቤት ጥያቄዎችን በበለጠ የመመለስ ተግባራት በትኩረት እንደሚከናወኑ አመላክተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የጽንፈኛው ሃይል አመራሮችና አባላት የሰላም ጥሪውን ተቀብለው መግባት ቀጥለዋል
Feb 23, 2026 118
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የጽንፈኛው ሃይል አመራሮችና አባላት መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ በመቀበል መግባት መቀጠላቸውን በመከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ አስታወቀ። እዙ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው የሰላምን አማራጭ የተቀበሉት የቡድኑ አመራሮችና አባላት በጎጃም ቀጣና የሚንቀሳቀሱ ናቸው። ለጥምር ጦሩ እጅ የሰጡት የጽንፈኛው ቡድን አመራሮችና አባላት መርዓዊ ከተማ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የቡድኑ አመራሮችና አባላት የገቡት 1 ፒ ኬ ኤም/መትረየስ ፣ 11 ክላሽ፣ 2 ኤስኬስ፣ 2 ፋል፣ 4 ቦንብ፣ 1 የመገናኛ ሬዲዮን ጨምሮ የተለያየ መሳሪያ ጥይቶችንና ካዝናዎችን በመያዝ ነው። በሰላም ከገቡትና በተለያየ ደረጃ ላይ ከሚገኙት 22 አመራሮችና አባላት መካከል አስር አለቃ ቻላቸው አስናቀ(ቻቻ) ፣ ቢኒያም ጋሻው፤ ጋሻው መኳንንት ፣ዘላለም አዱኛ ፣እንዳላማው ገብሬ እና ጋሻ ታደለ የተባሉ አመራሮች እንደሚገኙበት ተገልጿል።
ዛሬ በዲፕሎማሲው መስክ እያየን ያለነው ስኬት ሁሉ፣ ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ያላትን የተገቢነት ቦታ ዳግም ያረጋገጠ ነው
Feb 23, 2026 100
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ዛሬ በዲፕሎማሲው መስክ እያየን ያለነው ስኬት ሁሉ፣ ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ያላትን የተገቢነት ቦታ ዳግም ያረጋገጠ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ንጋት ከድምጽ አሰሚነት ወደ ተሰሚነት! የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ መዝገብ ሲገለጥ የሚነበበው በክብር የቆመ የታሪክ መሠረት፣ ነገር ግን እንደ ጥንታዊነቷ ድምጿ ጎልቶ የማይሰማበት የቆየ አሠራር ነበር። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው ድል ግን ይሄንን የተገደበ ተሳትፎ በመስበር፣ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ መድረክ ዋነኛ ተዋናይ ያደረገ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።   የለውጡ መንግሥት ዲፕሎማሲን እንደ ሀገራዊ ሉዓላዊነት መጠበቂያ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ብልጽግና ምንጭ በመቁጠር በብርቱ ሠርቷል። ዛሬ የዚህ ብልህ ዲፕሎማሲያዊ ሥራ ፍሬ እያፈራ፣ የሰላም እና የትብብር ጥረቱ አዝመራ እየታጨደ ነው፡፡ ለዚህ ሥር ነቀል ለውጥና ኢትዮጵያን በጎረቤት ሀገራት እና በአህጉር ደረጃ ያላትን አቀራራቢ ሚና በማጠናከር፣ የቀጣናውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የነበረውን የቆየ እሳቤ መቀየር ተችሏል። ሀገርን ማዕከል ያደረገ፣ ክብሯን እና ጥቅሟን የሚያስከብር ተለዋዋጭ ዲፕሎማሲ በመከተል ለተገኘው ስኬት ደግሞ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ቁልፍ መሐንዲስ ናቸው። የኢትዮጵያ ወደ BRICS+ መቀላቀል፣ በአፍሪካ ኅብረት እና በተባበሩት መንግሥታት መድረኮች ላይ የሚቀነቀነው አቋሟ፣ እንዲሁም በዓለም አቀፍ መሪዎች ዘንድ ያገኘችው ከፍ ያለ ተቀባይነት የዚሁ የጠራ ራዕይ ውጤቶች ናቸው።   ዛሬ በዲፕሎማሲው መስክ እያየን ያለነው ስኬት ሁሉ፣ ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ያላትን የተገቢነት ቦታ ዳግም ያረጋገጠ ነው፡፡
ዓድዋ የኢትዮጵያውያን የጋራ ትርክት መሠረትና የጥቁር ሕዝቦች ድል ነው -ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ ረጋሳ
Feb 23, 2026 95
ባህርዳር ፣የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፡ - ዓድዋ የኢትዮጵያውያን የጋራ ትርክት መሠረትና የጥቁር ሕዝቦች ድል መሆኑን በመከላከያ ሰራዊት የምሥራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ ረጋሳ ገለጹ። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምሥራቅ እዝ እና የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አባላት 130ኛውን የዓድዋ ድል በዓል በባሕር ዳር ከተማ በውይይት አክብረዋል።   በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የምሥራቅ እዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ ረጋሳ፣ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውያን የጋራ ትርክት መሰረትና የመላው ጥቁር ህዝቦች የድል አሻራ መሆኑን ገልጸዋል። የዓድዋ ድል የአሸናፊነት ምሥጢር፤ ኢትዮጵያውያን ከዳር እስከ ዳር ለሀገራቸው ክብርና ሉዓላዊነት በጋራ መቆማቸው ነው ብለዋል። ይህ የጀግንነት ታሪክ ከሀገር አልፎ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የድል ብስራትና የታሪክ እጥፋት ያመጣ መሆኑንም አብራርተዋል። በዚህ ታላቅ ገድል የተረከብናትን ታላቅ ሀገር ክብሯንና ሉአላዊነቷን በጀግንነት ጠብቀን ማስቀጠል ችለናል፤ ተጠናክሮም ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያን እድገት የማይሹ የባዕዳንን ተልእኮ የተቀበሉ ባንዳዎችንና የጥፋት ተግባራቸውን ለመፈፀም የሚጥሩ ጽንፈኞችን ተከታትሎ ህግ የማስከበሩ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት በኢትዮጵያ ላይ ሊቃጡ የሚችሉ የትኛውንም ጥቃቶች መመከት የሚያስችል አስተማማኝ ቁመና ላይ መሆኑንም ገልጸዋል።  
የሴቶች አደረጃጀቶች በጠቅላላ ምርጫው የሴቶች ተሳትፎ እንዲጠናከር እየሰሩ ነው
Feb 23, 2026 95
መቱ፤ የካቲት 16/2018 (ኢዜአ)፡- ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የሴቶች ተሳትፎ እንዲጠናከር አበክረው እየሰሩ መሆናቸውን በኢሉባቦር ዞን የሚገኙ የሴቶች አደረጃጀቶች ገለጹ። የኢሉባቦር ዞን ሴቶች ፌዴሬሽን ሊቀመንበር ወይዘሮ ሀገሬ ሀብታሙ ለኢዜአ እንዳስታወቁት ፌዴሬሽኑ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን የሴቶች ተሳትፎንና ሚና ለማጉላት እየሰራ ነው። በዚህም የዞኑ ሴቶች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድሕረ-ምርጫ ሂደቶች በንቃት እንዲሳተፉ ለማድረግ የምርጫ ሥነ-ምግባር ትምህርቶችን በየደረጃው ለሚገኙ ሴቶች በመስጠት ግንዛቤ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገርን የመገንባት፤ መንግስትንም የመመስረት ትልቅ ሀገራዊ ጉዳይ በሆነው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶች ተሳትፎ ትልቅ ቦታ አለው ያሉት ወይዘሮ ሀገሬ፣ የዞኑ ሴቶች ለምርጫው ስኬታማነት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ፌዴሬሽኑ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል። የዞኑ ሴቶች ማሕበር ሊቀመንበር ወይዘሮ አባይነሽ ሙሉነህ በበኩላቸው፣ የዞኑ ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማህበሩ በየደረጃው ግንዛቤ የማስፋት ስራ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይ የሴቶችን አደረጃጀቶች በማጠናከር በምርጫው ሂደቶች ውስጥ የመምረጥና የመመረጥ መብታቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ዋነኛ ተልዕኮችንን እየተወጣን ነው ብለዋል። በዚህ ረገድ ሴቶች በምርጫው በእውቀት ላይ የተመሠረተ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የግንዛቤ ማሳደጊያ መድረኮችን በማዘጋጀት ትምህርት በመስጠት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። የህዝቡን የልማት ፍላጎትን ይበልጥ ለማሟላትና ሀገራችን የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ ከማጠናከር ረገድ አደረጃጀቶቹ ለምርጫው ስኬታማነት የጀመሯቸውን ተግባራት አጠናክረው መቀጠላቸውን አስታውቀዋል። በተለይ ሴቶች ከአጠቃላይ የሕዝብ ብዛት ውስጥ ካላቸው ቁጥር ልክ በማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎአቸውን ለማሳደግ እንዲቻል ጠቅላላ ምርጫው ወሳኝነት እንዳለው የዞኑ የሴቶች አደረጃጀት አመራሮቹ አረጋግጠዋል።    
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አከራካሪ የሆኑ ምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ውሣኔ አስተላለፈ
Feb 23, 2026 89
አዲስ አበባ፤የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአማራ እና በትግራይ ክልላዊ መንግሥታት አከራካሪ የሆኑት ምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ውሣኔ አስተላለፈ። የምርጫ ቦርድ የውሳኔ ሐሳብ እንደሚከተለው ቀርቧል፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሠሌዳ ላይ በተመለከተው መሠረት ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም. የመራጮች ምዝገባ ለማካሄድ እየተዘጋጀባቸው ያሉትን ምርጫ ክልሎችና ምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር ለሕዝብ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ይህንኑ ቦርዱ ያወጣውን የምርጫ ክልሎችና ጣቢያዎች ዝርዝር ተከትሎ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም. የፌዴሬሽን ምክር ቤት በቁጥር ፌደም/አፌ/5/13138 ለቦርዱ በጻፈው ደብዳቤ በትግራይ እና በአማራ ክልላዊ መንግሥታት መካከል አከራካሪ ሆነው የቆዩት የአምስት ምርጫ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄው እስከሚፈታ የሁመራ፣ የአዲረመፅ፣ የኮረም አፍላ፣ የጠለምትና የራያ አላማጣ ምርጫ ክልሎች ከትግራይ ክልላዊ መንግሥት ውጪ ሆነው ለብቻቸው በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲደረግ ምክር ቤቱ መወሰኑን ለቦርዱ አሳውቋል። የክልል ምክር ቤት ምርጫው በአካባቢዎቹ ላይ የተነሳው የይገባኛል ውዝግብ በሕገ-መንግሥት ውሳኔ ሲፈታ አመቺ ጊዜ ተመርጦ ወደፊት እንዲካሄድ መወሰኑንም እንዲሁ ምክር ቤቱ አሳውቋል። በመሆኑም ቦርዱ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ መሠረት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከላይ በተጠቀሰው አግባብ ለመፈጸም የሚያስችለውን ሕግና ሥርዓት በመጠበቅ ተግባራዊ የሚያደርግ መሆኑን ያስታውቃል።
የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ ዓላማ ትናንትን በማከም ነገን የተሻለ ማድረግ  ነው - ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)
Feb 23, 2026 132
ቦንጋ፤ የካቲት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ ዓላማ ትናንትን በማከም ነገን የተሻለ ማድረግ ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ምልክቱን(የስንዴ ነዶ) እና ማኒፌስቶ የማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በቦንጋ ከተማ አካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለፁት የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ አላማ በሀገረ መንግስቱ ግንባታ ሂደት ውስጥ ያጋጠመውንና ትናንትን በማከም ነገን የተሻለ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል።   በኢኮኖሚው ዘርፍ ያጋጠመውን የተዛባ መዋቅራዊ ችግር በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ለመፍታት ፓርቲው ባደረገው ጥረት ባለፉት ዓመታት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ለአብነት አንስተዋል። በዚህም በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት በአለም እውቅና የተሰጠውን ድል ማስመዝገቡን ጠቅሰው የዘመናት ቁጭት የነበረውን የህዳሴ ግድብ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት አብቅቷል ብለዋል። በክልሉም የግብርና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ፣ የገቢ አቅምን ለማሳደግ እንዲሁም በስራ ዕድል ፈጠራና በሌሎችም ዘርፎች በተደረጉ ሰፊ ርብርቦች በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡ በማህበራዊ ዘርፍም የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ተወዳዳሪና ብቁ ትውልድን መፍጠርና ጤናማ ትውልድን ለማፍራት የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ ናቸው ብለዋል፡፡ በዚህም የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር እንደሀገር የተያዘውን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ በክልሉ ያሉ አቅሞችን ለይቶ የማልማት ስራ በትኩረት እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡   በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፤ የብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉና ሀገርን የሚያሻግሩ ውጤቶች ማስመዝገቡን ገልጸዋል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልም ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተደረገው ርብርብ ፍሬ እያፈራ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም የህዝቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አንስተው በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ ድሎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር ለማድረግ መንገዱ ብልፅግና ነው ብለዋል። በመርሃ ግብሩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
በሕዝብና በመንግሥት መካከል የተፈጠረው ጠንካራ ትብብር ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት የጎላ ሚና ተጫውቷል
Feb 23, 2026 84
ገንዳ ውኃ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን በሕዝብና በመንግሥት መካከል የተፈጠረው ጠንካራ ትብብር ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት የጎላ ሚና መጫወቱን የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ። በአካባቢው የተፈጠረው ሰላም ለረጅም ጊዜ ተዘግተው የነበሩ የትራንስፖርት መስመሮች ዳግም አገልግሎት መስጠት እንዲጀምሩ አስችሏል። የመምሪያው ኃላፊ ደረሰ አዱኛ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በዞኑ የመጣው ሰላም የሕዝቡና የፀጥታ አካላት የነቃ ተሳትፎና ቁርጠኝነት ውጤት ነው። አመራሩ ያለ ሕዝብ ድጋፍ ዘላቂ ሰላም እንደማይመጣ በመገንዘብ ሕብረተሰቡን ያሳተፈ ሥራ መስራቱንና በዚህም በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ማሕበረሰቡ መቀላቀላቸውን ገልጸዋል። በዞኑ በተገኘው ሰላም ከገንዳ ውኃ-ጎንደርና ከገንዳውኃ-ቋራ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት በመሆናቸው የንግድና ማሕበራዊ እንቅስቃሴው እንዲቀላጠፍ ማድረጉንም አመልክተዋል። ሕዝቡ የአካበቢውን ሰላም በንቃት እንዲጠብቅ አደረጃጀቶች እየተጠናከሩ መሆኑንም ጠቁመዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ ነዋሪው ካሳሁን ጌታነህ፤ መንግሥት ሕዝቡ ለሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። እየታየ ያለውን ሰላም በዘላቂነት ለማጽናት ከፀጥታ አካላት ጎን በመሆን ድጋፋቸውን አጠናከረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ሌላኛዋ የከተማው ነዋሪ እህትነሽ ማለደ በበኩላቸው፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበርና ሰላሙ ዘላቂ እንዲሆን ከመንግሥትና ከፀጥታ አካላት ጋር ያላቸውን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሚጠበቅብንን እንወጣለን-የፖለቲካ ፓርቲዎች
Feb 23, 2026 175
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሚጠበቅብንን እንወጣለን ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ምርጫ ሀገርንና ህዝብን የሚመራ መንግስት መመስረት የሚያስችል ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ፣ ሂደቱ ነፃ፣ ፍትሀዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው ይፋዊ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ከምርጫው ዋና ዋና የዝግጅት መርኃ ግብሮች መካከል አንዱ የሆነው የዕጩዎች ምዝገባ እየተከናወነ ሲሆን በቀጣይም የመራጮች ምዝገባ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚከናወን ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) እና የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ(ነእፓ)በዘንድሮው ምርጫ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ሰፊ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ለኢዜአ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ አባል እና የምርጫ ማናጀር ኢዮብ መሳፍንት እንደተናገሩት፣ ፓርቲው መሰረታዊ የሚባሉ ቅድመ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።   በአሁኑ ወቅትም ዕጩዎቹን በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ለምርጫው የውድድር ዘመን የሚያገለግሉ ዝርዝር የማኒፌስቶ እና የፖሊሲ ሰነዶች ዝግጅት መጠናቀቁንም አስረድተዋል። የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ በበኩላቸው፣ ጠንካራ ሀገር እና መንግሥት የሚመሰረተው በዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት ብቻ መሆኑን ፓርቲው ያምናል ብለዋል። በዚህም ፓርቲው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ እስከ ታችኛው መዋቅሩ ድረስ አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።   ለዚህም በመላ ሀገሪቱ የሚወዳደሩ ዕጩዎችን የማስመዝገብ ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው የፓርቲውን ማኒፌስቶ የማስተዋወቅ ስራ በቅርቡ ለመጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን ገልፀዋል። ፓርቲው የሀገሪቱን ነባራዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን ከግንዛቤ ያስገባ ፖሊሲ ማዘጋጀቱንም ጨምረው ተናግረዋል። ፓርቲዎቹ የአካታችነት ጉዳይ ላይ ትኩረት በማድረግ የሴቶች፣ የወጣቶች እና የአካል ጉዳተኞችን ተሳታፊነት ለማረጋገጥ እየሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል። ምርጫ ሀገርንና ህዝብን የሚመራ መንግስት መመስረት የሚያስችል ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ፣ ሂደቱ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ፓርቲዎቹና አባሎቻቸው የሚጠበቅባቸውን ሚና እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳና አጠቃላይ ሂደቱ ላይ ሕግን ተከትለው በአርአያነት ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ጠቁመው የሲቪክ ማህበራትና ሌሎች ተቋማትም ስራቸውን በገለልተኝነት ማከናወን ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።
ፖለቲካ
የጽንፈኛው ሃይል አመራሮችና አባላት የሰላም ጥሪውን ተቀብለው መግባት ቀጥለዋል
Feb 23, 2026 118
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የጽንፈኛው ሃይል አመራሮችና አባላት መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ በመቀበል መግባት መቀጠላቸውን በመከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ አስታወቀ። እዙ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው የሰላምን አማራጭ የተቀበሉት የቡድኑ አመራሮችና አባላት በጎጃም ቀጣና የሚንቀሳቀሱ ናቸው። ለጥምር ጦሩ እጅ የሰጡት የጽንፈኛው ቡድን አመራሮችና አባላት መርዓዊ ከተማ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የቡድኑ አመራሮችና አባላት የገቡት 1 ፒ ኬ ኤም/መትረየስ ፣ 11 ክላሽ፣ 2 ኤስኬስ፣ 2 ፋል፣ 4 ቦንብ፣ 1 የመገናኛ ሬዲዮን ጨምሮ የተለያየ መሳሪያ ጥይቶችንና ካዝናዎችን በመያዝ ነው። በሰላም ከገቡትና በተለያየ ደረጃ ላይ ከሚገኙት 22 አመራሮችና አባላት መካከል አስር አለቃ ቻላቸው አስናቀ(ቻቻ) ፣ ቢኒያም ጋሻው፤ ጋሻው መኳንንት ፣ዘላለም አዱኛ ፣እንዳላማው ገብሬ እና ጋሻ ታደለ የተባሉ አመራሮች እንደሚገኙበት ተገልጿል።
ዛሬ በዲፕሎማሲው መስክ እያየን ያለነው ስኬት ሁሉ፣ ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ያላትን የተገቢነት ቦታ ዳግም ያረጋገጠ ነው
Feb 23, 2026 100
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ዛሬ በዲፕሎማሲው መስክ እያየን ያለነው ስኬት ሁሉ፣ ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ያላትን የተገቢነት ቦታ ዳግም ያረጋገጠ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ንጋት ከድምጽ አሰሚነት ወደ ተሰሚነት! የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ መዝገብ ሲገለጥ የሚነበበው በክብር የቆመ የታሪክ መሠረት፣ ነገር ግን እንደ ጥንታዊነቷ ድምጿ ጎልቶ የማይሰማበት የቆየ አሠራር ነበር። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዲፕሎማሲው ዘርፍ የተመዘገበው ድል ግን ይሄንን የተገደበ ተሳትፎ በመስበር፣ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ መድረክ ዋነኛ ተዋናይ ያደረገ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።   የለውጡ መንግሥት ዲፕሎማሲን እንደ ሀገራዊ ሉዓላዊነት መጠበቂያ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ብልጽግና ምንጭ በመቁጠር በብርቱ ሠርቷል። ዛሬ የዚህ ብልህ ዲፕሎማሲያዊ ሥራ ፍሬ እያፈራ፣ የሰላም እና የትብብር ጥረቱ አዝመራ እየታጨደ ነው፡፡ ለዚህ ሥር ነቀል ለውጥና ኢትዮጵያን በጎረቤት ሀገራት እና በአህጉር ደረጃ ያላትን አቀራራቢ ሚና በማጠናከር፣ የቀጣናውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የነበረውን የቆየ እሳቤ መቀየር ተችሏል። ሀገርን ማዕከል ያደረገ፣ ክብሯን እና ጥቅሟን የሚያስከብር ተለዋዋጭ ዲፕሎማሲ በመከተል ለተገኘው ስኬት ደግሞ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ቁልፍ መሐንዲስ ናቸው። የኢትዮጵያ ወደ BRICS+ መቀላቀል፣ በአፍሪካ ኅብረት እና በተባበሩት መንግሥታት መድረኮች ላይ የሚቀነቀነው አቋሟ፣ እንዲሁም በዓለም አቀፍ መሪዎች ዘንድ ያገኘችው ከፍ ያለ ተቀባይነት የዚሁ የጠራ ራዕይ ውጤቶች ናቸው።   ዛሬ በዲፕሎማሲው መስክ እያየን ያለነው ስኬት ሁሉ፣ ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ያላትን የተገቢነት ቦታ ዳግም ያረጋገጠ ነው፡፡
ዓድዋ የኢትዮጵያውያን የጋራ ትርክት መሠረትና የጥቁር ሕዝቦች ድል ነው -ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ ረጋሳ
Feb 23, 2026 95
ባህርዳር ፣የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፡ - ዓድዋ የኢትዮጵያውያን የጋራ ትርክት መሠረትና የጥቁር ሕዝቦች ድል መሆኑን በመከላከያ ሰራዊት የምሥራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ ረጋሳ ገለጹ። በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምሥራቅ እዝ እና የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አባላት 130ኛውን የዓድዋ ድል በዓል በባሕር ዳር ከተማ በውይይት አክብረዋል።   በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የምሥራቅ እዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ ረጋሳ፣ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውያን የጋራ ትርክት መሰረትና የመላው ጥቁር ህዝቦች የድል አሻራ መሆኑን ገልጸዋል። የዓድዋ ድል የአሸናፊነት ምሥጢር፤ ኢትዮጵያውያን ከዳር እስከ ዳር ለሀገራቸው ክብርና ሉዓላዊነት በጋራ መቆማቸው ነው ብለዋል። ይህ የጀግንነት ታሪክ ከሀገር አልፎ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የድል ብስራትና የታሪክ እጥፋት ያመጣ መሆኑንም አብራርተዋል። በዚህ ታላቅ ገድል የተረከብናትን ታላቅ ሀገር ክብሯንና ሉአላዊነቷን በጀግንነት ጠብቀን ማስቀጠል ችለናል፤ ተጠናክሮም ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያን እድገት የማይሹ የባዕዳንን ተልእኮ የተቀበሉ ባንዳዎችንና የጥፋት ተግባራቸውን ለመፈፀም የሚጥሩ ጽንፈኞችን ተከታትሎ ህግ የማስከበሩ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት በኢትዮጵያ ላይ ሊቃጡ የሚችሉ የትኛውንም ጥቃቶች መመከት የሚያስችል አስተማማኝ ቁመና ላይ መሆኑንም ገልጸዋል።  
የሴቶች አደረጃጀቶች በጠቅላላ ምርጫው የሴቶች ተሳትፎ እንዲጠናከር እየሰሩ ነው
Feb 23, 2026 95
መቱ፤ የካቲት 16/2018 (ኢዜአ)፡- ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የሴቶች ተሳትፎ እንዲጠናከር አበክረው እየሰሩ መሆናቸውን በኢሉባቦር ዞን የሚገኙ የሴቶች አደረጃጀቶች ገለጹ። የኢሉባቦር ዞን ሴቶች ፌዴሬሽን ሊቀመንበር ወይዘሮ ሀገሬ ሀብታሙ ለኢዜአ እንዳስታወቁት ፌዴሬሽኑ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን የሴቶች ተሳትፎንና ሚና ለማጉላት እየሰራ ነው። በዚህም የዞኑ ሴቶች በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድሕረ-ምርጫ ሂደቶች በንቃት እንዲሳተፉ ለማድረግ የምርጫ ሥነ-ምግባር ትምህርቶችን በየደረጃው ለሚገኙ ሴቶች በመስጠት ግንዛቤ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሀገርን የመገንባት፤ መንግስትንም የመመስረት ትልቅ ሀገራዊ ጉዳይ በሆነው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶች ተሳትፎ ትልቅ ቦታ አለው ያሉት ወይዘሮ ሀገሬ፣ የዞኑ ሴቶች ለምርጫው ስኬታማነት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ፌዴሬሽኑ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል። የዞኑ ሴቶች ማሕበር ሊቀመንበር ወይዘሮ አባይነሽ ሙሉነህ በበኩላቸው፣ የዞኑ ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማህበሩ በየደረጃው ግንዛቤ የማስፋት ስራ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይ የሴቶችን አደረጃጀቶች በማጠናከር በምርጫው ሂደቶች ውስጥ የመምረጥና የመመረጥ መብታቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ዋነኛ ተልዕኮችንን እየተወጣን ነው ብለዋል። በዚህ ረገድ ሴቶች በምርጫው በእውቀት ላይ የተመሠረተ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የግንዛቤ ማሳደጊያ መድረኮችን በማዘጋጀት ትምህርት በመስጠት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። የህዝቡን የልማት ፍላጎትን ይበልጥ ለማሟላትና ሀገራችን የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ ከማጠናከር ረገድ አደረጃጀቶቹ ለምርጫው ስኬታማነት የጀመሯቸውን ተግባራት አጠናክረው መቀጠላቸውን አስታውቀዋል። በተለይ ሴቶች ከአጠቃላይ የሕዝብ ብዛት ውስጥ ካላቸው ቁጥር ልክ በማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎአቸውን ለማሳደግ እንዲቻል ጠቅላላ ምርጫው ወሳኝነት እንዳለው የዞኑ የሴቶች አደረጃጀት አመራሮቹ አረጋግጠዋል።    
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አከራካሪ የሆኑ ምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ውሣኔ አስተላለፈ
Feb 23, 2026 89
አዲስ አበባ፤የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአማራ እና በትግራይ ክልላዊ መንግሥታት አከራካሪ የሆኑት ምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ውሣኔ አስተላለፈ። የምርጫ ቦርድ የውሳኔ ሐሳብ እንደሚከተለው ቀርቧል፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሠሌዳ ላይ በተመለከተው መሠረት ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም. የመራጮች ምዝገባ ለማካሄድ እየተዘጋጀባቸው ያሉትን ምርጫ ክልሎችና ምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር ለሕዝብ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ይህንኑ ቦርዱ ያወጣውን የምርጫ ክልሎችና ጣቢያዎች ዝርዝር ተከትሎ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም. የፌዴሬሽን ምክር ቤት በቁጥር ፌደም/አፌ/5/13138 ለቦርዱ በጻፈው ደብዳቤ በትግራይ እና በአማራ ክልላዊ መንግሥታት መካከል አከራካሪ ሆነው የቆዩት የአምስት ምርጫ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄው እስከሚፈታ የሁመራ፣ የአዲረመፅ፣ የኮረም አፍላ፣ የጠለምትና የራያ አላማጣ ምርጫ ክልሎች ከትግራይ ክልላዊ መንግሥት ውጪ ሆነው ለብቻቸው በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲደረግ ምክር ቤቱ መወሰኑን ለቦርዱ አሳውቋል። የክልል ምክር ቤት ምርጫው በአካባቢዎቹ ላይ የተነሳው የይገባኛል ውዝግብ በሕገ-መንግሥት ውሳኔ ሲፈታ አመቺ ጊዜ ተመርጦ ወደፊት እንዲካሄድ መወሰኑንም እንዲሁ ምክር ቤቱ አሳውቋል። በመሆኑም ቦርዱ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ መሠረት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከላይ በተጠቀሰው አግባብ ለመፈጸም የሚያስችለውን ሕግና ሥርዓት በመጠበቅ ተግባራዊ የሚያደርግ መሆኑን ያስታውቃል።
የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ ዓላማ ትናንትን በማከም ነገን የተሻለ ማድረግ  ነው - ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)
Feb 23, 2026 132
ቦንጋ፤ የካቲት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ ዓላማ ትናንትን በማከም ነገን የተሻለ ማድረግ ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ። ብልፅግና ፓርቲ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ምልክቱን(የስንዴ ነዶ) እና ማኒፌስቶ የማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በቦንጋ ከተማ አካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለፁት የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ አላማ በሀገረ መንግስቱ ግንባታ ሂደት ውስጥ ያጋጠመውንና ትናንትን በማከም ነገን የተሻለ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል።   በኢኮኖሚው ዘርፍ ያጋጠመውን የተዛባ መዋቅራዊ ችግር በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ለመፍታት ፓርቲው ባደረገው ጥረት ባለፉት ዓመታት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ለአብነት አንስተዋል። በዚህም በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት በአለም እውቅና የተሰጠውን ድል ማስመዝገቡን ጠቅሰው የዘመናት ቁጭት የነበረውን የህዳሴ ግድብ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት አብቅቷል ብለዋል። በክልሉም የግብርና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ፣ የገቢ አቅምን ለማሳደግ እንዲሁም በስራ ዕድል ፈጠራና በሌሎችም ዘርፎች በተደረጉ ሰፊ ርብርቦች በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡ በማህበራዊ ዘርፍም የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ተወዳዳሪና ብቁ ትውልድን መፍጠርና ጤናማ ትውልድን ለማፍራት የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ ናቸው ብለዋል፡፡ በዚህም የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር እንደሀገር የተያዘውን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ በክልሉ ያሉ አቅሞችን ለይቶ የማልማት ስራ በትኩረት እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡   በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፤ የብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉና ሀገርን የሚያሻግሩ ውጤቶች ማስመዝገቡን ገልጸዋል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልም ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተደረገው ርብርብ ፍሬ እያፈራ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም የህዝቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አንስተው በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ ድሎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር ለማድረግ መንገዱ ብልፅግና ነው ብለዋል። በመርሃ ግብሩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
በሕዝብና በመንግሥት መካከል የተፈጠረው ጠንካራ ትብብር ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት የጎላ ሚና ተጫውቷል
Feb 23, 2026 84
ገንዳ ውኃ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን በሕዝብና በመንግሥት መካከል የተፈጠረው ጠንካራ ትብብር ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት የጎላ ሚና መጫወቱን የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ። በአካባቢው የተፈጠረው ሰላም ለረጅም ጊዜ ተዘግተው የነበሩ የትራንስፖርት መስመሮች ዳግም አገልግሎት መስጠት እንዲጀምሩ አስችሏል። የመምሪያው ኃላፊ ደረሰ አዱኛ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በዞኑ የመጣው ሰላም የሕዝቡና የፀጥታ አካላት የነቃ ተሳትፎና ቁርጠኝነት ውጤት ነው። አመራሩ ያለ ሕዝብ ድጋፍ ዘላቂ ሰላም እንደማይመጣ በመገንዘብ ሕብረተሰቡን ያሳተፈ ሥራ መስራቱንና በዚህም በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ማሕበረሰቡ መቀላቀላቸውን ገልጸዋል። በዞኑ በተገኘው ሰላም ከገንዳ ውኃ-ጎንደርና ከገንዳውኃ-ቋራ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት በመሆናቸው የንግድና ማሕበራዊ እንቅስቃሴው እንዲቀላጠፍ ማድረጉንም አመልክተዋል። ሕዝቡ የአካበቢውን ሰላም በንቃት እንዲጠብቅ አደረጃጀቶች እየተጠናከሩ መሆኑንም ጠቁመዋል። የገንዳ ውኃ ከተማ ነዋሪው ካሳሁን ጌታነህ፤ መንግሥት ሕዝቡ ለሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። እየታየ ያለውን ሰላም በዘላቂነት ለማጽናት ከፀጥታ አካላት ጎን በመሆን ድጋፋቸውን አጠናከረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ሌላኛዋ የከተማው ነዋሪ እህትነሽ ማለደ በበኩላቸው፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበርና ሰላሙ ዘላቂ እንዲሆን ከመንግሥትና ከፀጥታ አካላት ጋር ያላቸውን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሚጠበቅብንን እንወጣለን-የፖለቲካ ፓርቲዎች
Feb 23, 2026 175
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሚጠበቅብንን እንወጣለን ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ። ምርጫ ሀገርንና ህዝብን የሚመራ መንግስት መመስረት የሚያስችል ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ፣ ሂደቱ ነፃ፣ ፍትሀዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው ይፋዊ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ከምርጫው ዋና ዋና የዝግጅት መርኃ ግብሮች መካከል አንዱ የሆነው የዕጩዎች ምዝገባ እየተከናወነ ሲሆን በቀጣይም የመራጮች ምዝገባ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚከናወን ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) እና የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ(ነእፓ)በዘንድሮው ምርጫ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ሰፊ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ለኢዜአ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ አባል እና የምርጫ ማናጀር ኢዮብ መሳፍንት እንደተናገሩት፣ ፓርቲው መሰረታዊ የሚባሉ ቅድመ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።   በአሁኑ ወቅትም ዕጩዎቹን በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። ለምርጫው የውድድር ዘመን የሚያገለግሉ ዝርዝር የማኒፌስቶ እና የፖሊሲ ሰነዶች ዝግጅት መጠናቀቁንም አስረድተዋል። የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ በበኩላቸው፣ ጠንካራ ሀገር እና መንግሥት የሚመሰረተው በዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት ብቻ መሆኑን ፓርቲው ያምናል ብለዋል። በዚህም ፓርቲው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ እስከ ታችኛው መዋቅሩ ድረስ አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።   ለዚህም በመላ ሀገሪቱ የሚወዳደሩ ዕጩዎችን የማስመዝገብ ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው የፓርቲውን ማኒፌስቶ የማስተዋወቅ ስራ በቅርቡ ለመጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን ገልፀዋል። ፓርቲው የሀገሪቱን ነባራዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን ከግንዛቤ ያስገባ ፖሊሲ ማዘጋጀቱንም ጨምረው ተናግረዋል። ፓርቲዎቹ የአካታችነት ጉዳይ ላይ ትኩረት በማድረግ የሴቶች፣ የወጣቶች እና የአካል ጉዳተኞችን ተሳታፊነት ለማረጋገጥ እየሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል። ምርጫ ሀገርንና ህዝብን የሚመራ መንግስት መመስረት የሚያስችል ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ፣ ሂደቱ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ፓርቲዎቹና አባሎቻቸው የሚጠበቅባቸውን ሚና እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳና አጠቃላይ ሂደቱ ላይ ሕግን ተከትለው በአርአያነት ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ጠቁመው የሲቪክ ማህበራትና ሌሎች ተቋማትም ስራቸውን በገለልተኝነት ማከናወን ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።
ማህበራዊ
የፓስፖርት አገልግሎት በቅርብ ተደራሽ መደረጉ የዜጎችን እንግልት አስቀርቷል
Feb 23, 2026 63
ጎንደር፤ የካቲት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የፓስፖርት አገልግሎትን በአቅራቢያቸው ማግኘታቸው ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት እና ወጪ የሚያስቀር መሆኑን የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በጎንደር ከተማ በከፈተው ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ የፓስፖርት አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።   ከአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች መካከል አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪ ሶፍያ መሀመድ፣ ከዚህ ቀደም ፓስፖርት ለማግኘት ወደ ሌሎች ከተሞች በመሄድ ለከፍተኛ ወጪና ድካም ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል። አገልግሎቱ በቅርበት መጀመሩ ፓስፖርት ለማውጣት ወደ ሌሎች አካባቢዎች በመሄድ ይደርስ የነበረውን አላስፈላጊ ወጪና እንግልት ያስቀረ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላው የከተማው ነዋሪ ኤፍሬም ገበየሁ በበኩሉ፣ ፓስፖርት ለማውጣትና ለማደስ ወደ ሌላ አካባቢ መሄድ ግዴታ ስለነበር በተገልጋዩ ዘንድ ከፍተኛ ምሬት እንደነበር ገልጿል። አገልግሎቱ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በመክፈት ፓስፖርት መስጠት መጀመሩ እፎይታን የሰጠ ነው ብለዋል።   የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ ደብሬ የኋላ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በጎንደር ቅርንጫፍ መክፈቱ በአገልግሎት አሰጣጥ ህዝቡ ሲያነሳ የቆየውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የመለሰ ነው ብለዋል፡፡ የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የጎንደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አስቻለው እዘዘው እንደገለጹት፣ በአማራ ክልል በአምስት ከተሞች ቅርንጫፎችን በመክፈት አገልግሎት እየተሰጠ ነው። የጎንደር ቅርንጫፍም አገልግሎቱን ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ የዲጅታል አሰራር መጀመሩን ጠቁመው፣ 400 ለሚደርሱ አገልግሎት ፈላጊዎችም በአንድ ቀን ብቻ ፓስፖርት መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡   በአገልግሎት ማስጀመሪያ ሥነ-ስርአቱ ላይ የከተማው ከፍተኛ አመራሮችንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡  
የወጣቶች ሰብዕና ግንባታ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የጎላ ሚና አለው
Feb 23, 2026 64
ደብረብርሃን፤ የካቲት 16/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የወጣቶች ሰብዕና ግንባታ ላይ የተሰሩ ሥራዎች ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የጎላ ሚና እንዳላቸው የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። ''የወጣቶች መሪነት ለዘላቂ ሰላም'' በሚል መሪ ሃሳብ በወጣቶች ተጠቃሚነትና ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት በደብረ ብርሃን ተካሂዷል። የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ዘላለም አረጋ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፣ በክልሉ የወጣቶችን ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።   የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች፣ በከተማ ግብርና፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎች ዘርፎች እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች የወጣቱን ጥያቄ እየመለሱ ነው ብለዋል። ቢሮው የወጣቶችን ተሳታፊነትና ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማሳደግም በሥነ-ምግባርና ሰብዕና ግንባታ ላይ ያተኮረ ሥራ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ይህም ወጣቶች ለሰላም፣ ልማትና መልካም አስተዳደር መስፈን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ የወጣቶች ሰብዕና ግንባታ ላይ የተሰሩ ሥራዎች ለዘላቂ ሰላም የራሱን ሚና መጫወቱንም ገልጸዋል። በሥነ-ምግባር የታነጸ ወጣት በሀገሩ ጉዳይ ዘብ የሚቆም መሆኑን ጠቅሰው፣ ኢትዮጵያ በመጪው ግንቦት በምታከናውነው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍና ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።   የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፣ በዞኑ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋጋጥ በተደረገው ጥረት ወጣቱ ግንባር ቀደም ተሳታፊ ነው ብለዋል። በከተማዋ ሰላምን ለማጽናትና ልማቱን ለማስቀጠል ወጣቱ ከጸጥታ መዋቅር ጋር በትብብር መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። በውይይቱ ከተሳተፉ ወጣቶች መካከል ራሄል ይመር ወጣቱ ለሰላም ዘብ ከመቆም ጎን ለጎን የልማት ሥራዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ ነው። ወጣት ኤፍሬም ጎጨ በበኩሉ መንግስት ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራቱን አመልክቷል። በዚህም ወጣቶች በተመቻቸላቸው የመስሪያና የመሸጫ ቦታ እንዲሁም የብድር አቅርቦት ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች መትረፍ መቻላቸውን አንስቷል። የአካባቢን ሰላም በዘላቂነት ለማረጋገጥ የድርሻውን እንደሚወጣም አረጋግጧል።  
በወሰድነው ስልጠና ታግዘን የሚሰጠንን ግዳጅ ለመፈጸም ተዘጋጅተናል-የልዩ ሀይልና ጸረ-ሽብር አባላት
Feb 22, 2026 106
ሀዋሳ፤ የካቲት 15/2018(ኢዜአ)፦ በወሰድነው ስልጠና ታግዘን የሚሰጠንን ግዳጅ ለመፈጸም ተዘጋጅተናል ሲሉ በመከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የልዩ ሀይልና ጸረ-ሽብር ክፍል አባላት ገለጹ። የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዠ እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የመከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የተመሰረተበት 65ኛ ዓመት በዓል በሀዋሳ ተክብሯል። በስነስርዓቱ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ በመከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የልዩ ሀይልና የጸረ-ሽብር ክፍል አባላት እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ ድንበሯን የሚያስከብሩና ሰላሟን የሚያስጠብቁ ጠንካራ ጀግና ሰራዊት አላት። ጊዜውን መሰረት ያደረገና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የታጠቀ ሀይል ያላት ሀገራችን ምንም የሚበግራት ሀይል የለም ብለዋል። የልዩ ሀይልና ጸረ-ሽብር ክፍል አባል የሆኑት ምክትል አስር አለቃ አብረሀም ገዛኸኝ እንዳለው፥ ውትድርና የሚወደውና የሚያከብረው ሙያ በመሆኑ ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው። በዕዙ ስር ከመደበኛ እግረኛ አንስቶ እስከ ልዩ ሀይል ድረስ የተለያዩ ግዳጆችን መፈጸም የሚያስችለውን ስልጠና አግኝቷል። ኢትዮጵያ የብዙ ጀግኖች ወታደሮች እናት ናት ያለችው መሰረታዊ ወታደር ፋንታዬ ንጉሴ በስልጠና ላይ በነበረኝ ቆይታ በቂና ለማንኛውም ግዳጅ ብቁ የሚያደርገኝን ከመሰረታዊ የውትድርና ስልጠና በተጨማሪ የኮማንዶ ስልጠና ወስጃለሁ ብላለች። እኔ እያለሁ ሀገሬን ጠላት አይደፍራትም፤ በወሰድኩት ስልጠና በመታገዝ ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነኝ ብላለች። በወሰደችው ስልጠና የሚሰጣትን ግዳጅ በጥንካሬና በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን ተናግራለች። የልዩ ሀይልና የጸረ-ሽብር ክፍል ባልደረባ የሆነው አስር አለቃ ቾል ቶት በበኩሉ፥ ቀደም ሲል በተለያዩ ግዳጆች ተካፍሎ እንደነበርና አሁን በልዩ ሁኔታ ስልጠና በመውሰድ ኮማንዶ መሆን እንደቻለ ገልጿል። ሀገር ከሌለ እኔም የለሁም፣ ሀገር ማለት ህይወቴም ደሜም ነው ያለው አስር አለቃ ቾል፥ በርካታ የስልጠና ሂደቶችን በማለፍ ዛሬ ላይ እንደደረሰና በወሰደው ስልጠና በመታገዝ ለማንኛውም ግዳጅ ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል። ሰልጣኞች በወሰዱት ስልጠና ለሀገርና ለህዝብ ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸው በየብስ፣ በአየርና በባህር ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈጸም የሚያስችላቸውን አቅም እንደገነቡ ተናግረዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ከየካቲት 7 ጀምሮ በጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር፣ በወታደራዊ ትርኢትና ሌሎች መርሀ ግብሮች ሲካሄድ ቆይቶ ዛሬ የኢፌዴሪ ጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የማጠቃለያ ፕሮግራም ተከናውኗል። በዛሬው መርሃ ግብር የሰራዊቱ 44ኛ ኮርስ የኮማንዶ ምሩቃን ቀይ ቦኔታቸውን በመልበስ በይፋ የተመረቁ ሲሆን የክብር እንግዶች በተገኙበት የልዩ ዘመቻዎች እዝ የሰራዊቱ አባላት የወታደራዊ የሰልፍ ስነ ስርአት ተከናውኗል።
ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉም ዜጋ በሀገሩ ጉዳይ እኩል ተሳትፎ እንዲኖረው ዕድል የከፈተ ነው
Feb 22, 2026 95
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር አካታችነትን መሰረት በማድረግ ሁሉም ዜጋ በሀገሩ ጉዳይ እኩል ተሳትፎ እንዲኖረው የበለጠ ዕድል የከፈተ መሆኑን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ገለጸ። አካል ጉዳተኞች በሀገራዊ ምክክሩ በንቃት እንዲሳተፉ በማድረግ አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ ማስረከብ መቻሉንም ፌዴሬሽኑ ገልጿል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን መፍጠር የሚያስችል የምክክር አውድ ለመፍጠር በወሳኝ የምክክር ምዕራፍ ላይ ይገኛል። የምክክር ሂደቱም ዘላቂ ሀገራዊ ሰላምና ደኅንነትን በማጽናት ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ሚናው የጎላ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በቅርቡ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ለሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ የማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ መድረክ ላይ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች መሳተፋቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ ሁለንተናዊ ልማት ለማፋጠን በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ በመነጋገር መፍትሄ ማበጀት ያስፈልጋል ብለዋል። ለዚህም ቁልፉ መሳሪያ ኢትዮጵያውያን ተወያይተን ልንፈታቸው በሚገቡ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የመወያያ መድረክ ለመፍጠር የተጀመረውን ሀገራዊ ምክክር ወደ ውጤት በመቀየር ነው ብለዋል። ፌዴሬሽኑ ኮሚሽኑ ብሄራዊ ምክክሩን ለማድረግ አስቻይ ሁኔታን ለመፍጠር እስካሁን ባለፈባቸው ምዕራፎች የነቃ ተሳትፎ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቁመዋል። በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ በተደረጉ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቶች አካል ጉዳተኞች በንቃት እንዲሳተፉ የማድረግና አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ የማስረከብ ስራዎች ከተከናወኑ ተግባራት መካከል መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣይም ለሀገራዊ ምክክሩ ውጤታማነት ፌዴሬሽኑ አስተዋጽኦውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በዋናው የሀገራዊ ምክክር ላይ የሚሳተፉ አካል ጉዳተኞች ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መለየታቸውን ጨምረው ተናግረዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው የአምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን አንደኛ አስቸኳይ ስብሰባ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን ለስምንት ወራት ማራዘሙ ይታወቃል።
ኢኮኖሚ
የአምራች ኢንዱስትሪውን የምርት ተወዳዳሪነት የሚያጎለብት ምቹ ዕድል ተፈጥሯል
Feb 23, 2026 134
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአምራች ኢንዱስትሪውን የምርት ተወዳዳሪነትን የሚያጎለብት ምቹ የአሰራርና የድጋፍ አሰጣጥ ዕድል መፈጠሩን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር ዓባይ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ከተማ አቀፍ የ''ኢትዮጵያ ታምርት'' ንቅናቄ የፓናል ውይይት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሂዷል። የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎችና የኢንዱስትሪ ተዋንያን በተገኙበት በተካሄደው ፓናል ላይ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች በሰጡት አስተያየት፤ ኢትዮጵያ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ የምትሰጠው ትኩረት አስደናቂ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ታምርት ብሔራዊ ንቅናቄም ለዘርፉ ማነቆዎች መፍትሔ በመስጠት የምርታማነትን የሚያሳደግ እመርታዊ ውጤት እንዲመዘገብ እያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም የተቋማትን ቅንጅት በማጠናከር የአምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚ ዕድገት የሚኖረውን ድርሻ የሚያጎለብት የቦታና የፋይናንስ አቅርቦት ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል። የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ መኮንን ያኢ በተነሱ አስተያየትና ጥያቄዎች ላይ በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅምን ማሳደግ የሚያስችል ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል። በቀጣይም የተቋማትን ቅንጅት በማጠናከር አምራች ኢንዱስትሪዎች በመሬት አቅርቦት ላይ የሚነሷቸውን ጥያቄዎች አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ፋይናንሲንግ ምክትል ፕሬዝዳንት ጌታሰው ፋንታው፤ የኢንዱስትሪ ዕድገትን ለማስቀጠል የፋይናንስና የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ ነው ብለዋል። በጉሙሩክ ኮሚሽን የጉሙሩክ አሰራር ልማት ዳይሬክተር እንዳሻው ተመስገን በበኩላቸው፤ የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ በርካታ የሕግና የአሰራር ማሻሻያዎች መደረጋቸውን አስረድተዋል። የአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነትን ለማሳደግ የተደረጉ የአሰራር ማሻሻያዎች የድጋፍ ማዕቀፎችን በሚገባ በመጠቀም ምርታማነትን ማስቀጠል እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል። በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አብርሃም ደበበ (ዶ/ር)፤ የኢንዱስትሪ ምርታማነትን የሚያግዝ መፍትሔ አመላካች የጥናትና ምርምር ሥራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። በቀጣይም የአዲስ አበባ ኢንዱስትሪዎችን ምርታማነት ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት መፍትሔ አመላካች የምርምር ሥራዎችን በማከናወን ገንቢ ሚና እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። የውይይት መድረኩን ያጠቃለሉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር ዓባይ፤ ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ዕድገት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል። በዚህም በማሽነሪ ሊዝ፣ በፋይናንስና በማስፋፊያ መሬት አቅርቦት የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን የምርት ተወዳዳሪነትና ብቃት የሚያሻሽል ምቹ ምኅዳር መፈጠሩን ገልጸዋል። አምራች ኢንዱስትሪዎችም በሚደረግላቸው ድጋፍና ክትትል የምርትን ጥራትና በብዛት የማምረት አቅምን መገንባት እንደሚኖርባቸው አስረድተዋል።  
በመዲናዋ የ97 ሺህ ቤቶች ግንባታ እየተፋጠነ ነው -ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Feb 23, 2026 95
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ለመገንባት ከታቀደው 100 ሺህ ቤቶች ውስጥ የ97 ሺህ ቤቶች ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝ የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ከተማ አስተዳደሩ እያካሄደ ካለው ዘርፈ ብዙ ልማት ውስጥ ለቤት ልማት ልዩ ትኩረት መስጠቱን አመልክተዋል።     በ2018 ዓ.ም ለማከናወን ከታቀደው 100 ሺህ የቤቶች ግንባታ ዉስጥ የ97 ሺህ ቤቶች ግንባታ በአስደናቂ ሁኔታ እየተፋጠነ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል። በግንባታ ላይ ካሉ 17 ሳይቶች መካከል በገርጂ፣ በቱሉ ዲምቱ፣ በገላን ጉራ (የመጀመሪያና ሁለተኛ ምዕራፍ)፣ በአቃቂ ቃሊቲ (ወርቁ ሰፈር) እንዲሁም በንፋስ ስልክ ላፍቶ የገበያ ማዕከል እየተገነቡ ያሉትን ቤቶች አፈጻጸም ዛሬ መገምገሙን ጠቁመዋል። ግምግማ የተደረገባቸው ሳይቶች ፕሮጀክቶች ከተጀመሩ ከ6 እስከ 7 ወር ቢሆንም፣ ቀን እና ማታ ያለማቋረጥ በመስራት ፤ እጅግ ትጉ በሆኑ ኢትዮጵያዊ ኮንትራክተሮች፣ ማህበራት፣ አማካሪዎች፣ ትጉ አመራሮች እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ በአሁኑ ወቅት አበረታች ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል። በሳይቶቹ ከ200 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩንና በርካታ ኮንትራክተሮችና ማህበራት በአዲስ የሥራ ተነሳሽነትና በትጋት እየተሰሩ ይገኛል ነው ያሉት። የከተማ አስተዳደሩ ትኩረት የቤቶቹ ግንባታ ፍጥነት ብቻ ላይ ሳይሆን፣ ከቤት አቅርቦት የዘለለ በተሻሻለ ዲዛይን ጤናማ፣ ውብና ዘመናዊ የመኖሪያ መንደሮችን መገንባት ላይ ነው ብለዋል።   የግንባታ ጥራት ለማረጋገጥ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአማካሪነት ከከተማ አስተዳደሩ ጋር እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። እየተገነቡ ካሉት ቤቶች ውስጥ 50 ሺዎቹ በከተማው በጀት የሚገነቡ ሲሆን የተቀሩት 50 ሺዎቹ ደግሞ የሚገነቡት በመንግስትና የግል አጋርነት መሆኑን ጠቁመዋል። ከለውጡ በፊት እንደዚህ አይነት ሰፊ የቤት ልማት አይደለም በከተማው በጀትና በአንድ አመት ቀርቶ በተለመደው የባንክ ብድር እንኳን በየአምስት አመቱ 100 ሺህ ተሰርቶ ቢሆን ኖሮ ዛሬ በሚሊዮኖች ተመዝግበው ለረጅም አመታት እስከ ዛሬ የሚጠባበቁ እና ከ60 ቢሊዮን በላይ የኮንዶሚንዬም የቦንድ እዳን ተረክበን ለመክፈል እና ለማስተናገድ ባልተገደደን ነበር ብለዋል። አሁን እየተገነባ ያለው ቤት ከነዋሪዎች ሰፊ ፍላጎት አንጻር አቅርቦቱ ገና ቢሆንም፣ የቤት ችግርን በዘላቂነት የመፍታት ስራችን ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ከንቲባዋ በመልዕክታቸው ላይ ያሰፈሩት።
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ትንበያ ካሉ ተጨባጭ ውጤቶች የመነጨ ነው - የዘርፉ ምሁራን
Feb 23, 2026 95
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ትንበያ በመሬት ላይ ካሉ ተጨባጭ የልማት ሥራዎችና ስኬቶች የመነጨ መሆኑን የኢኮኖሚ ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት፤ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ የ10 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት እንደሚያስመዘግብ መግለጻቸው ይታወሳል። መንግሥት የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ በወሰዳቸው እርምጃዎች የዋጋ ንረትን ወደ ነጠላ አሃዝ በማውረድ ትልቅ ስኬት መመዝገቡንም አመልክተዋል፡፡ በዚህም የዋጋ ንረትን ወደ 9 ነጥብ 7 በመቶ ነጠላ አሃዝ በማውረድ ከፍተኛ ስኬት መመዝገቡን ጠቅሰው፥ አሁንም ብዙ መስራት ይጠበቃል ብለዋል። የኢኮኖሚ ምሁሩ ደረጄ ደጀኔ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ መንግሥት ተግባራዊ ያደረገው አጠቃላይ የኢኮኖሚ ሪፎርም ለታየው ተከታታይ ዕድገት መሠረት ሆኗል። በተለይም በግብርና ዘርፍ ባለፉት ስድስት ዓመታት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት በሆነው በዚህ ዘርፍ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ተመዝግቧል ብለዋል። በኢንዱስትሪው ዘርፍ "ኢትዮጵያ ታምርት" በተሰኘው ብሔራዊ ንቅናቄ የሀገር ውስጥ አምራቾች አቅም እንዲጠናከርና የገቢ ምርቶች በሀገር ውስጥ እንዲተኩ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየታዩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በማዕድን ልማት ዘርፉ ሌላው አስደናቂ ውጤት እየተመዘገበበት ያለ የኢኮኖሚ ምንጭ መሆኑን ጠቁመው የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት የሀገሪቱን ዕድገት እያረጋገጡ መሆናቸው የዘንድሮው የ10 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ትንበያ ስኬታማ እንደሚሆን ማሳያ ነው ብለዋል።   የኢኮኖሚ ምሁር ጀማል መሐመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ቀውስ ባለበት ወቅት ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለው ዕድገት ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል። ይህ ዕድገት ለወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ አዳዲስ የኢንቨስትመንት መስኮችን ለማስፋፋት እና ሌሎች ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን እንደሚያግዝ አስታውቀዋል። የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ውጤት እያመጡ መሆኑንና ግሽበቱን ወደ ነጠላ አሃዝ ዝቅ ማድረግ መቻሉ አስደናቂ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥት የኤክስፖርት ገቢን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ መቻሉ የሀገሪቱን የዕዳ ጫና ለመቀነስ ትልቅ ሚና እንደተጫወተ ምሁራኑ አስረድተዋል። ይህም በቀጣይ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጨማሪ የፋይናንስ አቅም እንደሚፈጥር አመልክተዋል። አሁን እየተወሰዱ ያሉ የፖሊሲ እርምጃዎች ተጠናክረው ከቀጠሉ፣ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዓመታት የላቀ የብልጽግና ደረጃ ላይ እንደምትደርስ ምሁራኑ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።    
ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ውጤት እያመጡ ነው
Feb 23, 2026 84
አዳማ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የከተማና መሰረት ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለፁ። ሚኒስቴሩ የ2018 በጀት አመት የስድስት ወራት የሴክተር ስራዎች አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የክልሎች የዘርፉ አመራሮችና የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአዳማ ከተማ እያካሄደ ነው። ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በወቅቱ እንደገለፁት በለውጡ መንግስት ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው።   የከተማ ነዋሪዎች ህይወት ከመለወጥ፣ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ፣ የመሬት አስተዳደር ስርዓት ከማዘመንና የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ችግሮች ከማቃለል አኳያ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል። የከተሞችን መሰረተ ልማት በማስፋፋትና ዲጂታል አገልግሎትን ተደራሽ ከማድረግ አንፃር ተስፋ ሰጪ ተግባራት መከናወናቸውንም አመልክተዋል። በተለይ የኮሪደር ልማት በከተሞች መሰረተ ልማት ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ገፅታቸውን በመቀየር በኩል ተጨባጭ ለውጦች የተገኘበት መሆኑን ተናግረዋል። በኮሪደር ልማቱ የመደመር መንግስት እሳቤዎች ውጤት የታየበትና የከተሞች የገፅታ ለውጥ ያየንበት ነው ሲሉም አክለዋል።   በዚህም ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን በጥራትና በፍጥነት የማጠናቀቅ አቅም ባህል እየሆነ የመጣበት መሆኑን ጠቁመው ልማቱ የህዝብና የመንግስት ትብብር የታየበት እንደሆነም አንስተዋል። በከተሞች የተገልጋዩን ህብረተሰብ ዕርካታ ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመው የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንና ከተሞች ለኑሮና ለስራ ምቹ እንዲሆኑ ከማድረግ አኳያ ተስፋ ሰጪ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። አረንጓዴ ልማቱም የከተሞችን ውበት ከማስጠበቅ ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር እንደቻለም ሚኒስትሯ ጠቅሰዋል። በቀሪው ሁለተኛው ግማሸ በጀት ዓመት ዲጂታል አገልግሎትን ማስፋፋት፣ በተለያዩ ከተሞች እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ማጠናቀቅ፣ የውበትና አረንጓዴ ልማት ስራዎችን ማጠናከር፣ የመኖሪያ ቤት ጥያቄዎችን በበለጠ የመመለስ ተግባራት በትኩረት እንደሚከናወኑ አመላክተዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የሳይንስ ሙዚየም ለኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ምርምር ዕድገት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው
Feb 23, 2026 86
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የሳይንስ ሙዚየም ለኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ምርምር ዕድገት ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ኪሩቤል መንበሩ ገለጹ። የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ማህበር አባላት እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሳይንስ ሙዚየምንና በሳይንስ ሙዚየም የሚገኘውን የጠፈር ምርምር ማዕከል (ፕላኔታሪየም) ጎብኝተዋል። በዚህም የከዋክብት ምልከታ፣ የጠፈር ሳይንስ ገለጻ እንዲሁም የጠፈር ምርምር ማዕከል የጠፈር ዘጋቢ ፊልም ተመልክተዋል።   የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ኪሩቤል መንበሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የሳይንስ ሙዚየሞች በአንድ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ ጉልህ አዎንታዊ ተፅዕኖ ያሳርፋሉ። ይህ የሳይንስ ሙዚየም ማህበረሰቡ ስለ ሳይንስ ያለው አረዳድና እውቀት እንዲያድግ ከማድረጉም በላይ ለዘርፉ ያለውን ቀረቤታ ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል። በአዲስ አበባ የተገነባው የሳይንስ ሙዚየም በውስጡ በያዛቸውና ሳይንስን በቀላሉ ማስረዳት በሚያስችሉ ኤግዚቢሽኖች አማካኝነት ለዘርፉ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።   ሙዚየሙ በተለይም ታዳጊዎችና ወጣቶች ለሳይንስ ቅርብ እንዲሆኑ ከማድረጉ ባለፈ በትምህርት የቀሰሙትን ዕውቀት በተግባር አይተው እንዲረዱ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል። ማህበሩ በአቅም ግንባታ፣ በመሰረተ ልማት እና ታዳጊዎች በዘርፉ ያላቸውን ዕውቀት እንዲያጎለብቱ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። ማህበሩ ለሁሉም ክፍት መሆኑን በመጥቀስ፣ ፍላጎቱ ያላቸው ታዳጊዎችና ወጣቶች አባል በመሆን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል።   የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ማህበር የውጭ ጉዳዮች አስተባባሪ ክብረት አጽብሀ በበኩሉ፣ የጉብኝቱ ዓላማ በስፔስ ሳይንስ የሚከናወኑ ስራዎችን ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ገልፀዋል። ሳይንስ ሙዚየሙ ታዳጊዎችና ወጣቶች ወደ ዘርፉ እንዲቀላቀሉ መንገድ ከመጥረጉ ባለፈ፣ ተመራማሪዎች ሥራዎቻቸውን ለኅብረተሰቡ ተደራሽ እንዲያደርጉ ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም ተናግሯል።   ጉብኝቱ ስለጠፈር እውቀት እና ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው የገለጹት ደግሞ ተማሪ ፍትህ ግርማ እና ጽዮን ብርሀኑ ናቸው። የሳይንስ ሙዚየሙ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተለየ በአሁኑ ወቅት ለዘርፉ የተሰጠውን ልዩ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ ነው
Feb 21, 2026 116
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢዲ ኮኔክት ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የ2026 የኢትዮ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ሳይንስ እና የትምህርት ፌስቲቫል ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።   ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ የመክፈቻ መርሐ ግብር ላይ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮችና ተማሪዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፤ በዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን ወጣቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለሀገሪቱ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ መሠረት መሆኑን ጠቁመው ፌስቲቫሉ ወጣቶች በትምህርት ልቀውና በሳይንስ መሪ መሆን እንዲችሉ ዓለም አቀፍ ልምድ ካላቸው ተቋማት ጋር ምህዳር እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ ከአጋር አካላት ጋር በመሆን የወጣቶችን የፈጠራ ስራ የሚያጎለብት "የሰመር ካምፕ" ለማዘጋጀት ማቀዱን ይፋ አድርገዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው፣ የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ በሰው ሀብት ልማት ላይ መስራት ቀዳሚ ተግባር ነው ብለዋል፡፡   ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ሥራዎች እንደ አማራጭ የሚታዩ ሳይሆን ለዘመናዊ ስልጣኔ መሰረት የሆኑ የልማት ምሰሶዎች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። የአፍሪካ ህብረት የጤና፣ ሰብአዊ መብቶች እና ማህበራዊ ልማት ኮሚሽነር አምባሳደር ሚንአታ ሳማቴ ሴሱማ፣ የወጣቶች ተሳትፎ ለአጀንዳ 2063 ስኬት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የዩኔስኮ የሰላም ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ጋይ ጆከን በበኩላቸው አፍሪካ ያላትን የወጣት ኃይል ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ እንደ ትልቅ ስትራቴጂካዊ ሀብት ሊወሰድ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢድ ኮኔክት ኢትዮጵያ መስራች ኢንጂነር ሳሙኤል ንጉሴ እንዳሉትም፤ ተቋማቸው ተማሪዎችን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሰራል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ የታደሙት ተማሪ ካይረን ግርማ እና ሲፈን ዮሃንስ በበኩላቸው፣ መድረኩ የትምህርት ዕድሎችን ለማግኘትና ዓለም አቀፍ እውቀትን ለመቅሰም ትልቅ በር እንደከፈተላቸው መስክረዋል። ፌስቲቫሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገውን የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ግቦች ከማሳካት አንጻር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና መሰረት የሚጥል ነው
Feb 21, 2026 114
ደሴ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡-ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥል መሆኑን የወሎ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። የአካል ጉዳተኞችን የፈጠራ አቅም በማጎልበት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ታዳጊዎች ለፈጠራና ለክህሎት እንዲጠቀሙበት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ይገባል ኢትዮጵያ የበለጸገ ኢኮኖሚ ባለቤት ለመሆን በምታደርገው ጥረት ውስጥ ቴክኖሎጂ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። የሀገሪቷን የ5 ዓመት የቴክኖሎጂ ልማት ጉዞ የሚመራበት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ወደ ሥራ ከገባ ሰነባብቷል። የስትራቴጂው ትግበራ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት በማፋጠን ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የወሎ ዩኒቨርስቲ ምሁራን ያነሳሉ። የዲጂታል ኢትዮጵያ ትግበራ በዋናነት የመንግስት አገልግሎቶችን በማዘመን፣ ብልሹ አሰራርን በመከላከልና ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል።   የወሎ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ሀዋ ወሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በየዘርፉ የተጀመሩ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራሮች ሥራን ከማቅለልና አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባለፈ ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ረገድ ተስፋ ሰጪ ውጤት እያስመዘገቡ ነው። ዩኒቨርሲቲው ይህንን ሀገራዊ ግብ ለማሳካት ቴክኖሎጂን የማስፋፋት፣ የማላመድና የጥናትና ምርምር ስራዎችን በትኩረት የማከናወን ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ጠቁመዋል። ተመራቂ ተማሪዎች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎትን እንዲታጠቁ በማድረግ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር የሥራ እድሎች ተጠቃሚ የሚሆኑበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነው ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የኢንፎርሜሽን ሲስተም መምህር ታደሰ ቢራራ በበኩላቸው፤ ሀገሪቱ ለዘርፉ የሰጠችው ትኩረት በ2030 የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል።   በቴሌ ብር፣ ሞባይል ባንኪንግ፣ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያና በ"ኢትዮ ኮደርስ" ስልጠናዎች የታየው ስኬት አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባለፈ ብልሹ አሰራርን መከላከልና ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባት እያስቻለ ነው ብለዋል። ግብርናን፣ ቱሪዝምንና ንግድን ከቴክኖሎጂ ጋር ማስተሳሰር መቻሉ ለሀገሪቷ ሁለንተናዊ እድገት መፋጠን መሰረት የሚጥል መሆኑንም ነው ያብራሩት። በገጠር አካባቢዎች የኢንተርኔትና የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት የቴክኖሎጂ ተደራሽነትን ማስፋትና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል። ወሎ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂን የተላመደ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራትና የሕብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
የአካል ጉዳተኞችን የፈጠራ አቅም በማጎልበት ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል
Feb 21, 2026 96
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የአካል ጉዳተኞችን የፈጠራ አቅም በማጎልበት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተመላከተ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ "አካል ጉዳተኝነትን የሚያካትት ማህበረሰብ ለተሻለ ማህበራዊ ዕድገት" በሚል መሪ ሃሳብ 34ኛውን ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን በወላይታ ሶዶ ከተማ በተለያዩ ኹነቶች እያከበረ ይገኛል።   የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ካሰች ኤልያስ በወቅቱ እንዳሉት፤ የአካል ጉዳተኞች አካታችነትን በማጠናከር ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል። በአካል ጉዳተኞች ላይ የሚደርሱ አሉታዊ አመለካከቶችን በማስወገድ አቅማቸውን እንዲያወጡ የተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ውጤት ማሳየቱንም ጠቁመዋል። በዚህም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነታቸው እንዲያድግ እንዲሁም ድምፃቸው እንዲሰማ አርአያ ለሆኑ አካል ጉዳተኞች ዕውቅና የመስጠት እንዲሁም ተሞክሮአቸውን የማሸጋገር ተግባር ይጠናከራል ብለዋል።   በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቦጋለ ፈይሳ፤ አካል ጉዳተኞች አስፈላጊው ድጋፍ ከተደረገላቸው የፈጠራ አቅማቸውን በማውጣት ተጠቃሚ ሊሆኑ እንደሚችሉ ገልጸዋል።   በክልሉ የሚገኙ አካል ጉዳተኞች በርካታ ስራዎችን እየሰሩ መሆናቸውን በማንሳት እምቅ አቅማቸውን እንዲያወጡ ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ፤ አካል ጉዳተኞች ያላቸውን የፈጠራ እና የትምህርት ዕውቀት ለማውጣት ያለውን የአመለካከት ችግር ማረም ይገባል ብለዋል።   የለውጡ መንግስት ለአካል ጉዳተኞች የሰጠው ልዩ ትኩረት ተጠቃሚነታቸው እንዲያድግ ማድረጉንም ጠቁመዋል:: የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካል ጉዳተኞች ማህበራት ህብረት ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ደነቀ ዳጮ፤ በክልሉ የአካል ጉዳተኞችን ሰብዓዊ መብት በማስከበር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።   በመሆኑም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለውጥ አምጪ ፕሮግራሞችን በመቅረጽና ተሳትፏቸውን በማሳደግ አካል ጉዳተኞችን ሊደግፉ እንደሚገባም ገልጸዋል። በመድረኩ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የአካል ጉዳተኞች ማህበራት ተወካዮች ተገኝተዋል።
ስፖርት
በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታዎች
Feb 24, 2026 50
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ ዛሬ አራት የመልስ ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ማንችስተር ዩናይትድ ኤቨርተንን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ አራተኛ ከፍ አደረገ ምሽት አምስት ሠዓት ላይ ኢንተር ሚላን ከቦዶ ግሊምት በሳን ሲሮ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ቦዶ ግሊምት 3 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ኢንተር ሚላን ወደ ጥሎ ማለፍ ለመግባት ከሁለት ጎል በላይ ልዩነት ማሸነፍ ይኖርበታል። ተጋጣሚው ቦዶ ግሊምት ማሸነፍ፣ አቻ መውጣት እና በአንድ የግብ ልዩነት መሸነፍ 16ቱን መቀላቀል ያስችለዋል። በሌላኛው መርሐ-ግብር ኒውካስትል ዩናይትድ ከካራባግ ምሽት አምስት ሠዓት ላይ በሴይንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በመጀመሪያው ጨዋታ 6 ለ 1 ያሸነፈው ኒውካስትል ዩናይትድ የማለፍ እድሉ እጅጉን ሰፊ ነው። በአንጻሩ ተጋጣሚው ካራባግ በሂሳባዊ ስሌት ወደ ጥሎ ማለፍ የመግባት እድሉ በጣም የጠበበ ነው። ባየር ሌቨርኩሰን ከኦሎምፒያኮስ ምሽት አምስት ሠዓት ላይ በቤይአሬና ስታዲየም ይጫወታሉ። የጀርመኑ ባየር ሌቨርኩሰን በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ከሜዳው ውጪ 2 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ውጤቱንም ተከትሎ የማለፍ እድሉን አስፍቷል። የግሪኩ ኦሎምፒያኮስ ወደ ጥሎ ማለፍ ለመግባት ከሁለት ጎል በላይ ልዩነት ማሸነፍ አለበት። ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ አትሌቲኮ ማድሪድ ከክለብ ብሩዥ በዋንዳ ሜትሮፖሊታኖ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሁለቱ ክለቦች ባለፈው ሳምንት ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ ሶስት አቻ ተለያይተዋል። የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፈው ቡድን ጥሎ ማለፍ ይገባል።
ማንችስተር ዩናይትድ ኤቨርተንን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ አራተኛ ከፍ አደረገ
Feb 24, 2026 77
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/ 2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሐ-ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በሂል ዲኪንሰን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ተቀይሮ የገባው ቤንጃሚን ሼሽኮ በ71ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። በጨዋታው ላይ ኤቨርተን የተሻሉ የግብ እድሎችን ቢፈጥርም የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የነበረው ማንችስተር ዩናይትድ ያገኘውን አጋጣሚ ወደ ግብ በመቀየር አሸናፊ ሆኗል። የዩናይትዱ ግብ ጠባቂ ሴን ላመንስ የጨዋታው ኮከብ ተጫዋች ሆኖ ተመርጧል። በሊጉ 13ኛ ድሉን ያስመዘገበው ማንችስተር ዩናይትድ በ48 ነጥብ ደረጃውን ከአምስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለመሳተፍ በሚያደርገው ፉክክር ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝቷል። እንግሊዛዊው ጊዜያዊ አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ በሊጉ አምስተኛ ድሉን አሳክቷል። ቡድኑ በካሪክ ስር እስከ አሁን አልተሸነፈም። በአንጻሩ በሊጉ 10ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ኤቨርተን በ37 ነጥብ 9ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወሳኝ ድል አሳክቷል 
Feb 23, 2026 61
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሸገር ከተማን 3 ለ 2 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ረድኤት አስረሳኸኝ ሁለት ግቦችን ስታስቆጥር እፀገነት ግርማ ቀሪዋን ጎል ለንግድ ባንክ ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ሰናይት ኡራጎ እና ገነሜ ወርቁ ለሸገር ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በውድድር ዓመቱ 11ኛ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ35 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። የወቅቱ የሊጉ ዋንጫ አሸናፊ ንግድ ባንክ ከሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ አድርጓል። በአንጻሩ በሊጉ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሸገር ከተማ በ27 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ዛሬ በተደረገ ሌላኛው መርሐ-ግብር ሃዋሳ ከተማ እና አዳማ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ጨዋታዎቹን ተከትሎ 14ኛ ሳምንት ተጠናቋል። የ15ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከየካቲት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የበልግ እርሻ እንቅስቃሴን ቀድመው የሚጀምሩ አካባቢዎች፣ በሚቀጥሉት ስምንት ቀናት የሚኖረውን የእርጥበት አየር ሁኔታ በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል 
Feb 23, 2026 68
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦የበልግ እርሻ እንቅስቃሴን ቀድመው የሚጀምሩ አካባቢዎች፣ በሚቀጥሉት ስምንት ቀናት የሚኖረውን የእርጥበት አየር ሁኔታ በአግባቡ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አሳሰበ። ኢንስቲትዩቱ ከየካቲት 14 እስከ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የሚኖረውን የአየር ሁኔታ አስመልክቶ ለኢዜአ በላከው መግለጫ፤ በሚቀጥሉት ቀናት በበልግ አብቃይ አካባቢዎች ላይ አንጻራዊ የእርጥበት ሁኔታ እንደሚኖር ገልጿል። በተለይም በደቡብ ምዕራብ፣ በደቡብ እና በመካከለኛው ዝቅተኛ አካባቢዎች የሚታየው እርጥበት፤ ለአፈር ዝግጅት፣ ለዘር ዝግጅትና ለዘር መዝራት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ብሏል። የሚገኘው እርጥበት ለግጦሽ ሳር በቀል፣ ለቋሚ ተክሎች እድገትና ለሰውና ለእንስሳት የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማሻሻል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም አመልክቷል፡፡ በላይኛው አዋሽ፣ በላይኛውና በመካከለኛው ባሮ አኮቦ፣ በኦሞ ጊቤ፣ በስምጥ ሸለቆ እንዲሁም በጥቂቱ በላይኛው ገናሌ ዳዋ ተፋሰሶች ላይ ከመካከለኛ እስከ መጠነኛ ዝናብ እንደሚጠበቅም ተመላክቷል፡፡ በዚህም ምክንያት በተጠቀሱት ተፋሰሶች ላይ መጠነኛ የገፀ-ምድር ውሃ ፍሰት እንደሚኖር ተመላክቷል። በሌላ በኩል የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑት የደቡብ እና የደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች ላይ ደረቃማ ቀናት እንደሚስተናገዱ በመግለጫው ተጠቅሷል።    
የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የቡና ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ረገድ ትልቅ ለውጥ ፈጥሯል
Feb 23, 2026 165
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የቡና ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ረገድ ትልቅ ለውጥ ፈጥሯል ሲሉ የዘርፉ ተዋናዮች ገለጹ። ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት 469 ሺህ ቶን ቡና ለዓለም ገበያ በመላክ 2 ነጥብ 65 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቷ የሚታወስ ሲሆን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት 600 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጪ በመላክ ከሦስት ቢሊየን ዶላር በላይ ለማግኘት አቅዳ እየሰራች ትገኛለች፡፡ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት በግብርናው ዘርፍ የቡና ምርታማነት ላይ አመርቂ ውጤት ለማስመዝገብ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ወሳኝ መሆኑን ያረጋግጣሉ።   በኦሮሚያ ክልል የቡና አልሚና ላኪ የሆኑት አቶ ፈጠነ የኋላሸት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ በተለይ አረንጓዴ አሻራ ትልቅ አስተዋጾ ማበርከቱን ተናግረዋል ባለፉት ዓመታትም የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር በተከታታይነት መከናወኑ ቡናን ለማምረት ተስማሚ ሥርዓተ ምህዳርና የአየር ሁኔታ እንዲኖር ማስቻሉን ነው ያነሱት። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በቡና መስክ ላይ የተሰማሩት አንዷለም ፋንታ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ ለውጥ እያመጣ ነው ብለዋል።   ይህም በመሆኑ በአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ላይ የማህበሩ አባላት በስፋት በመሳተፍ ልማቱን እያገዝን እንገኛለን ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል። በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የቡና ምርታማነታችንን ለማሳደግ የአካባቢውን የተፈጥሮ ገጽታ መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በሲዳማ ክልል በቡና አቅራቢነት የተሰማሩት አባተ ኪሾ ናቸው ።   አስተያየት ሰጪዎቹ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን እና ዝርያዎችን ለተከላ ለማዘጋጀት የሚያስችላቸውን ተግባር እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡና ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ዘሪሁን ቃሚሶ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ሀገራችን ከቡናው ዘርፍ ማግኘት የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማሳለጥ ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።   አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እንደ ሀገር ማከናወን ከጀመርን በኋላ ከ8 ቢሊየን በላይ የቡና ችግኞች መተከላቸውን አስታውቀዋል።    
የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ባህል የማድረግ እንቅስቃሴ
Feb 22, 2026 88
አዲስ አበባ፤የካቲት 15/2018(ኢዜአ)፦በመዲናዋ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ባህል የማድረግ እንቅስቃሴ በጎ አድራጎት ያለምንም ክፍያና ጎትጓች ለህሊና እርካታ ለሰዎች የሚከወን የዕለት ተዕለት ተግባር ነው። በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ባህል በማድረግ በቤት እድሳት፣ በደም ልገሳ፣ ማዕድ በማጋራትና በሌሎች ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ከፕሎጊንግ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በእንጦጦ ፓርክ ያዘጋጀው የጽዳትና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር ተካሂዷል።   በዚህ መርሃ ግብር ላይ ከሁሉም የከተማዋ ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ በጎ ፈቃደኞች ተሳትፈዋል። የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አስራት ንጉሴ በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት በጎ ፈቃደኝነት ለራስ የህሊና እርካታን ከመስጠት ባለፈ፣ ጠንካራና የተሳሰረ ማህበረሰብ ለመገንባት ቁልፍ ሚና አለው። የከተማ አስተዳደሩ ይህንን ተግባር የዜጎች የዘወትር ባህል ለማድረግ ባለፉት ዓመታት ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመው፤ በዚህም በከተማዋ በርካታ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደረጉ የበጎ ፈቃድ ስራዎች መከናወናቸውን አስታውቀዋል፡። በአሁኑ ወቅት በሙያቸውና በጉልበታቸው ለሀገራቸው ለህዝባቸው የሚደርስ ማህበረሰብ መፍጠር መቻሉን አንስተው፤ ይህ ንቁ ትውልድ የመፍጠር ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። እንደ ፕሎጊንግ ኢትዮጵያ ሁሉ ህብረተሰቡም ሆነ ሌሎች አካላት ብዙ ጥቅም በሚያስገኘው በጎ ፍቃድ በመሳተፍ ሀገሩንና ወገኑን ማገልገል ይገባዋል ብለዋል፡። የፕሎጊንግ ኢትዮጵያ መስራች ፕሮፌሰር ፍሬው ከፍያለው በበኩላቸው፤ አካባቢን መንከባከብ የሁሉም ዜጋ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን አስታውቀዋል።   ድርጅታቸው ላለፉት አምስት ዓመታት የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ከጽዳት ጋር በማቀናጀት (Plogging) በየሳምንቱ የፕላስቲክ ቆሻሻዎችን የመሰብሰብ ዘመቻ ሲያከናውን መቆየቱን አስታውሰዋል። ዝቅ ብሎ ቆሻሻን ማንሳት ለራስ ክብርንና ከፍታን ይሰጣል ያሉት ፕሮፌሰሩ ማህበረሰቡ ይህንን ልምድ እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።   በዕለቱ በጽዳት ዘመቻው ላይ የተሳተፉት በጎ ፈቃደኞች ፍቅር ግርማ እና ካሱ መገርሳ በሰጡት አስተያየት፤ በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ በመሳተፋቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው፤ በቀጣይም ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።        
በዞኑ የለሙ ተፋሰሶች በሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ ኢኮኖሚያዊ አቅማችንን አሳድገውልናል-ተጠቃሚዎች 
Feb 21, 2026 155
አርባ ምንጭ ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- በጋሞ ዞን የለሙ ተፋሰሶች ምርትና ምርታማነትን ከማረጋገጥ ባለፈ በሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ አኮኖሚያዊ አቅማቸውን ማሳደጉን በዞኑ የሚገኙ ተጠቃሚዎች ገለፁ። በምስራቅ ሸዋ ዞን ከ119 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ዕቀባ ሥራ እየተከናወነ ነው ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ወደ ትርፍ ምርት- የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት በዞኑ በበጀት ዓመቱ ወደ 160 ሺህ ሄክታር በሚጠጋ መሬት ላይ የተፋሰስ ልማት እየተከናወነ መሆኑም ተመላክቷል። ተጠቃሚዎቹ እንደገለፁት፤ በዞኑ የለሙ ተፋሰሶች ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ በሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ ኢኮኖሚያዊ አቅማችንን አሳድጎልናል ብለዋል። አርሶ አደር ሚሊዮን በየነ በዞኑ የቁጫ ወረዳ ነዋሪ ናቸው፤ በአካባቢያቸው ከዚህ ቀደም በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች የተጎዳ መሬት ሲያገግም፣ የጠፋ ምንጭ ዳግም ሲፈልቅ እና የአካባቢው ስነ-ምህዳር ወደ ልምላሜ ሲቀየር በዓይናቸው ተመልክተዋል። አመቺ ባለመሆናቸው ለእርሻ ስራ ጥቅም ላይ ሳይውሉ የቆዩ የእርሻ ማሳዎች ጥቅም ላይ ውለው ወደ ምርታማነት ተቀይረው ሲመለከቱ ደግሞ እውን ሳይሆን ህልም መስሏቸውም ያውቃል። አሁን ላይ በተፋሰስ ልማት ስራው በለማው መሬት ላይም በእንስሳት እርባታና በንብ ማነብ ስራ ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ መሆን ጀምረዋል።   ለውጡንም በማየታቸው በዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ስራ ላይ ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆን ብቻም ሳይሆን ቤተሰባቸውንም በማስተባበር እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል። በአርባ ምንጭ ከተማ የ"ነህሚያ የእንስሳት እርባታ ማህበር" ሰብሳቢ ወጣት ህዝቅኤል ኦሎባ የማህበሩ አባላት የተፋሰስ ልማቱ በፈጠረላቸው ጸጋ ተነሳስተው ባለፈው ዓመት በሦስት ላሞች እና በሁለት ኮርማዎች ሥራ መጀመራቸውን አስታውሷል። በተፋሰሱ በለማው ቦታ ላይም መንግስት ባመቻቸላቸው ብድር ለእንስሳት መኖ በማምረት ተጠቃሚነታቸው እየጨመረ መሆኑንም ጠቅሷል። በአሁኑ ወቅት ከላሞቹ አምስት ጥጃዎችን ማግኘታቸውን የጠቀሰው ወጣቱ ለተለያዩ አካላት የወተት ምርት በማቅረብ የገቢ ምንጫቸው ማደጉን አስረድቷል፡፡ በአካባቢው የተከናወነው የተፋሰስ ልማት ጥሩ የስራ ዕድል ይዞልን መጥቷል ያለው ደግሞ በዞኑ ምዕራብ አባያ ወረዳ በአንኮበር ቀበሌ "የጦይሎ ንብ አንቢዎች ማህበር" ሰብሳቢ ወጣት አለማየሁ ቶጋ ነው። ማህበሩ በ2014 ዓ.ም እንደተመሰረተ የሚናገረው አለማየሁ በለማው ተፋሰስ ላይ በአንድ በኩል ንብ እያነቡ በሌላ በኩል የለማው ከባቢ እንዳይጎዳ ጥበቃ በማድረግ ላይ እንገኛለን ብሏል። መንግስት 30 ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን፣ አንድ የማር ማጣሪያ ማሽንና መስሪያ አልባሳት እንዳበረከተላቸው ገልጾ አስፈላጊው የሙያ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም አልሸሸገም። ''በዓመት ከ3 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ ማር እየሸጥን ራሳችንን ከመቻል ባለፈም ቤተሰቦቻችንን እያገዝን እንገኛለን'' ብሏል።   የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ወርቅነህ ካልሳ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ የተፋሰስ ልማት በተለያየ መልክ የዞኑን ህዝብ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል። የተጎዳ መሬትን እንዲያገግም በማድረግ ብሎም ስነ-ምህዳርን በማስተካከል ምርትና ምርታማነት እንዲረጋገጥ በማስቻል የአርሶ አደሮችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል። ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጋር በተያያዘ የነዋሪዎች ግንዛቤ እየሰፋ በመምጣቱ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ጋር ተዳምሮ ምርት በስፋት እየተመረተ ይገኛል ብለዋል። በያዝነው በጀት ዓመትም በ336 ንዑስ ተፋሰሶች 160 ሺህ ሄክታር በሚጠጋ መሬት ላይ የተፋሰስ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውንም አቶ ወርቅነህ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ አጋርነታቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
Feb 23, 2026 71
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ሳዑዲ አረቢያ በሰላም፣ ልማት እና ዲፕሎማሲ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ(ኢ/ር) ከተመራ ልዑክ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ አፍሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ ለረጅም ጊዜ የቆየ እና ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸው ትብብሩ በጥልቅ የባህል፣ የኢኮኖሚና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ላይ የተመሰረተ መሆኑን አውስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ በአፍሪካ ያላትን ዘላቂ ትብብር እና በአህጉሪቱ እያደገ የመጣውን ኢንቨስትመንት አልፎም በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ያላትን ገንቢ ሚና አድንቀዋል።   ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመቀናጀት በሊቢያ፣ ሱዳን እና ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች እያሳየች ያለውን የዲፕሎማሲ ድጋፍ እና ተሳትፎ አዎንታዊ መሆኑን አመልክተዋል። የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ ቢን አብዱልከሪም ኤል- ከሀርጂ በበኩላቸው የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ በልማት፣ በሰላም እና በባለብዙ ወገን ትብብር ያለውን የመሪነት ሚና አንስተዋል። ሳዑዲ አረቢያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ልማት፣ ሰላም፣ ደህንነት እና ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላትን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች የአፍሪካ ህብረትና ሳዑዲ አረቢያ ያላቸውን ግንኙነት በጋራ መከባበር መንፈስ፣ በወዳጅነት እና በስትራቴጂካዊ አጋርነት ላይ በመመስረት የበለጠ ለማጠናከር የጋራ ፍላጎት ማሳየታቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና የፈጠረውን የንግድ ትስስር ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት ወሳኝ ነው
Feb 21, 2026 123
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን የንግድ ትስስር ዕድል በአግባቡ ለመጠቀም በመንግሥታትና በግሉ ዘርፍ መካከል ያለ አጋርነትን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ።   የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የስምምነቱ ትግበራ የንግድ መሰናክሎችን በማስቀረት የሀገራትን የንግድ ልውውጥ ለማሳለጥ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተ ነው። እስካሁን 50 ሀገራት ፈርመው ያጸደቁት ይህ የንግድ ቀጣና፤ በዲጂታል የኢኮኖሚ ዕድገት የፋይናንስ ቴክኖሎጂን በማስፋት የአኅጉሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በማዘመንና የገንዘብ ዝውውርን በማቀላጠፍ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት የአሰራር ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተዳራሽ ለማድረግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ዘርግቷል የኢትዮጵያ ቱሪዝም አዲሱ ገጽታ፤ ከአማራጭ ማጣት ወደ መዳረሻዎች ብዛት በኢትዮጵያ ለግል ዘርፉ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ ኢኮኖሚው እየተነቃቃ ነው የአፍሪካን የተፈጥሮ ሃብትም በተሻለ የኢንቨስትመንት ተወዳዳሪነት በማልማት የመሰረተ ልማት፣ የዋጋ ግሽበትና የንግድ መሰናክሎችን ለመቀነስ አይነተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም አስረድተዋል።   በዚህም አባል ሀገራት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን በማፋጠን የእርስበርስ የንግድ ልውውጥን ማሳለጥ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት የፈጠረውን ዕድል ለመጠቀም የግሉ ዘርፍና የአባል ሀገራት መንግሥታት የእርስ በርስ የንግድ ልውውጥን ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሰረትም የአባል ሀገራት ኢንቨስትመንትን የሚያነቃቃ የኢንቨስትመንት ጥበቃ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስረድተዋል። የስምምነቱ የኢንቨስትመንት ጥበቃም የአፍሪካን በመተማመን ላይ የተመሰረተ የእርስበርስ ንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ለማጎልበት የሚያስችል መሆኑን አስታውቀዋል።
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና የቱርክዬ ታሪካዊ አጋርነት 
Feb 16, 2026 338
የኢትዮጵያ እና ቱርኪዬ ግንኙነት ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የአፍሪካ ጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ ኦቶማን ኢምፓየርን ጨምሮ በታሪክ ከመካከለኛው ምስራቅ እና አውሮፓ ጋር ታሪካዊ ግንኙነት ነበራት። ኦቶማን ኢምፓየር ለዘመናዊቷ ቱርክዬ መሰረት ጥሎ አልፏል። በ20ኛ ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት በዲፕሎማሲ እና ንግድ ልውውጥ ላይ የተመረኮዘ ነው። ቱርክዬ አፍሪካን እንደ ስትራቴጂካዊ አጋር የምትቆጥር ሲሆን አፍሪካ ህብረትን ጨምሮ ቁልፍ አህጉራዊ ተቋማት የሚገኙባት እና የአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ የዚህ ትብብር አካል ናት። ኢትዮጵያ እና ቱርክዬ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ 1896 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የመጀመሪያ የኦቶማን-ቱርክዬ ቆንስላ ጽህፈት ቤት እ.አ.አ በ1912 በሐረር ከተማ ተከፍቷል። ቱርክዬ ከሰሃራ በታች የመጀመሪያውን ኤምባሲ የከፈተችው በኢትዮጵያ ሲሆን ወቅቱም እ.አ.አ በ1926 ነበር። ኢትዮጵያ በቱርክዬ ኤምባሲዋን የከፈተችው እ.አ.አ በ1933 ነው። ያለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያ እና የቱርክዬ ግንኙነት ከፍተኛ እድገት ያሳየበት ነው። ኢኮኖሚ የሁለቱ ሀገራት አጋርነት ምሰሶ እንደሆነ ይጠቀሳል። የቱርክዬ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጨርቃ ጨርቅ፣ በግንባታ እና በግብርና ማቀነባበሪያ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ተሰማርተው ይገኛሉ። ቱርክዬ በኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ካላቸው ሀገራት መካከል በዋናነት ትጠቀሳለች። የሀገራቱ የንግድ ግንኙነትም እየዳበረ መጥቷል። ከኢኮኖሚ ባሻገር ፖለቲካ፣ ደህንነት፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንዱስትሪ እና ባህል ሌሎች የትብብር መስኮች ናቸው። ባለፉት 10 ዓመታት በሁለቱ ሀገራት መካከል የከፍተኛ ባለስልጣናት የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። የቱርክዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን እ.አ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ጉብኝቱ የሀገራቱን የሁለትዮሽ ትስስር ማጠናከርን ያለመ ነው። እ.አ.አ በ2017 የቀድሞ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በቱርክዬ ጉብኝት በማድረግ ኢትዮጵያን በመወከል በቱርክዬ-አፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ላይ ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እ.አ.አ በ2021 በቱርክዬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ ሀገራቱ በተለያዩ ዘርፎች የትብብር ስምምነቶች መፈራረማቸው ይታወሳል። ውሃ፣ ወታደራዊ ትብብር እና ፋይናንስ ከስምምነቶቹ ትኩረቶች መካከልም ይገኙበታል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የተደረገው ኢትዮጵያና ቱርክዬ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበት 125ኛ ዓመት ላይ መሆኑ ልዩ ትርጉም የሚሰጠው ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት የተፈረሙት ስምምነቶች የግንኙነቱን መጠናከር እንደሚያመለክቱ ገልጸዋል። ለኢትዮጵያ የልማት እና መረጋጋት ጉዞ ቱርክዬ የምታደርገውን ድጋፍም አድንቀዋል። የቱርክዬ መንግስት እና ህዝብ ያደረገልንን የወሳኝ ጊዜ ትብብር ሀገራችን ኢትዮጵያ መቼም አትረሳውም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ በነበራቸው ቆይታ። የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እ.ኤ.አ በ2021 በቱርክዬ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ አዲስ የተገነባውን የኢትዮጵያ ኤምባሲም መርቀዋል። የቱርክዬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እ.አ.አ በ2024 ኢትዮጵያን በመጎብኘት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የከፍተኛ ባለስልጣናቱ ጉብኝት የሀገራቱን የግንኙነት መጠናከር የበለጠ የሚያጎለብቱም ናቸው። ኢንዱስትሪ እና ማኑፋክቸሪንግ፣ መሰረተ ልማት፣ የንግድ ብዝሃነትን ማስፋት፣ መከላከያ እና ደህንነት፣ ቱሪዝም እና ባህል ሀገራቱ ትብብራቸውን ሊያሰፉባቸው እየሰሩባቸው ከሚገኙ መስኮች መካከል ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ እና የቱርክዬ አጋርነት በጋራ ፍላጎቶች፣ ተራማጅ በሆኑ ሀሳቦች፣ በጋራ ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እና እየተለወጡ ያሉ የዓለም እውነታዎችን ባማከለ ሁኔታ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። በልማት ጎዳና ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ እና ቱርክዬ ከአፍሪካ ጋር ያላት ትስስር የሁለቱን ሀገራት ስትራቴጂካዊ ትብብር የበለጠ ጥልቀት የሚሰጥ ነው። ሁለቱ ሀገራት በፍጥነት እየተለዋወጠ በሚገኘው ቀጣናዊ እና የዓለም ምህዳር ውስጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ለማጠናከር እየሰሩም ይገኛሉ።
የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋርነታቸውን ለማደስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለጹ
Feb 16, 2026 166
አዲስ አበባ፤ የካቲት 9/2018(ኢዜአ):- የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የአህጉሪቱን የፋይናንስ መዋቅር ማጠናከርን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት በአዲስ መልክ ለማደስ እንደሚሰሩ አስታወቁ። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሂዷል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከጉባኤው ጎን ለጎን ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ(ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ባንኩ ለአፍሪካ ቁልፍ የትኩረት መስኮች እያደረገ ያለውን ጠንካራ ድጋፍ ያደነቁ ሲሆን ለአፍሪካ ልማት ፈንድ 11 ቢሊን ዶላር ተጨማሪ ገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን መልካም የሚባል እርምጃ መሆኑን አመልክተዋል። ሊቀመንበሩ እና የባንኩ ፕሬዝዳንት ከእዳ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የደህንነት ፈተናዎች ባለፈ የፋይናንስ አቅርቦት የአፍሪካ አበይት ፈተና መሆኑን በምክክራቸው ወቅት ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች የፕሮጀክት ዝግጅት ትብብርን ለማጠናከር፣ የአንድ ትሪሊን የአሜሪካን ዶላር የአፍሪካ ካፒታል ማሰባሰብ፣ የአፍሪካ የብድር ምዘና ኤጀንሲን ማጎልበትና ጠንካራ የአፍሪካ የፋይናንስ ስርዓት መገንባት ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በውይይቱ የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋርነታቸውን በአዲስ መልክ ለማደስ ተሠማመተዋለ። በዓመት ሁለት ጊዜ ለመወያያት እና በአፍሪካ ፋይናንስ ላይ የከፍተኛ ደረጃ ምክክር ለማካሄድ እቅድ መያዛቸውንም ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሐተታዎች
   የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 159
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን።   የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው።   የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል።   የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት።   የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች
Jan 25, 2026 606
የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ ፍላጎት በመገንዘብ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያልዘነጉ የቦረና ቅን ልቦች። ዶክተር አብዱራህማን ሮኔ ይባላሉ። ትውልድና ዕድገታቸው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልተሌ በተሰኘ አካባቢ ነው። የቀለም ትምህርት በሀገር ቤት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ሀገረ አሜሪካ በማቅናት ኑሯቸውን በዚያው አድርገዋል። ለበርካታ ዓመታት ሕይወታቸውን በአሜሪካን ሀገር እየመሩ የሚገኙት ዶክተር አብዱራህማን ከሁለት ዓመታት በፊት ለቤተሰብ ጥየቃ ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ቦረና አቀኑ። የጉዟቸው ዓላማ ለዓመታት የናፈቋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ብቻ እንደነበር ያስታውሳሉ።   በቤተሰብ ጥየቃ ቆይታቸውም በቦረና ዞን ተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የሚጎበኙበት አጋጣሚ ተፈጠረ። ጉብኝታቸውም ሆስፒታሉ በኪነ-ሕንፃ የተዋበ መሆኑን ነገር ግን የህክምና ግብዓት እጥረት ያለበት ሆኖ ማግኘታቸውን ይናገራሉ። በተልተሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ምልከታቸው በሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች ሲቸገሩ ማየታቸው የወቅቱ አሳዛኝ ትውስታ እንደነበርና ይህን እጥረት ወደ አሜሪካን ሀገር ሲመለሱ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መወሰናቸውን አስታውሰዋል። ዶክተር አብዱረሃማን በተልተሌ አካባቢ ተወልደውና አድገው ለሕክምና ባለሙያነት ያበቃቸውን ትምህርት የቀሰሙ ሰው በመሆናቸው በሆስፒታሉ የተመለከቱት የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት የሺዎችን ሕይወት የሚታደግ ሰብዓዊ ፕሮጀክት የሚቀረጽበት ሃሳብ እንዲወለድ ምክንያት ሆኗል። ከዚያም የራሳቸውን የሕክምና ሙያ ዕውቀትና በውጭ ያካበቱትን ግንኙነት በመጠቀም መነሻቸውን ባለፈው ዓመት ለተልተሌ እና ሜጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በድጋፍ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመትም የሞያሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ ለሶስት ትላልቅ የጤና ተቋማት ዘመናዊ ሕክምና መሳሪያዎችን አበርክተዋል። እነኚህ የሕክምና መሳሪያዎች አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ያስታወሱበት በጎ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ያስተማራቸውን ማህበረሰብ በማስታወስ መንግስት የዜጎችን የሕክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል። ሌላኛው በአሜሪካን ሀገር በሕክምና ሙያ የሚያገለግሉት ዶክተር ዋቆ ዳደቻ በበኩላቸው፤ ሁሉም ዜጋ በትብብር መስራት ከቻለ የማህበረሰብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል ይላሉ። ይህ የሆስፒታሎችን የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት ለማሟላት የሚደረገውን ተሳትፎ ሁሉም በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎች ሊማሩበት የሚገባ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የሕክምና ተቋማትን ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ አሳድጎ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ማሰብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ በውጭ የሚኖሩ የሕክምና ሙያተኞች የሚያደርጉት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ በአርዓያነት የሚወሰድ ነው ብለዋል። በዶክተር አብዱራህማን መሪነት ለቦረና አካባቢ ሆስፒታሎች የተደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍም የተቋማቱን የጤና አገልግሎት ጥራት በማስጠበቅ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በመግለጽ። በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህዝባቸውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በማገዝ በኩል የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 943
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 870
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 1012
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 969
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 1520
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3835
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3487
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2317
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8108
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6594
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60329
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54289
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34882
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32448
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27659
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26681
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26200
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25951
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60329
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54289
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34882
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32448
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ ዐሻራ ከዓድዋ - እስከ አፍሪካ ኅብረት
Feb 14, 2026 279
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የፖለቲካ፣ የታሪክ እና ዲፕሎማሲ ምኅዳር ውስጥ ልዩ ስፍራ እና ተጽዕኖ ያላት ሀገር ናት። የጥንታዊ ሥልጣኔዎች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ፤ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ የአፍሪካ ሀገር ከመሆኗ ባሻገር ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ መስፋፋት ትልቅ ሚና ተጫውታለች። ይህንም ታሪክ ይዘክራል። 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ዛሬ ይጀመራል አይበገሬነት፣ ሉዓላዊነት እና የፓን አፍሪካ መንፈስ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ካሳረፈቻቸው ዐሻራዎች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። በዘመናዊው ዓለምም በአፍሪካ አጀንዳዎች ላይ ወሳኝ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነጻነት እና ማንነት ተምሳሌት ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1896 በዓድዋ ጦርነት በጣሊያን ኃይሎች ላይ የተቀዳጀችው ድል በአፍሪካ እና በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ የሚሰጠው ነው።   አብዛኛው የአፍሪካ አኅጉር በቅኝ ግዛት ውስጥ በነበረበት ወቅት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ድል ሉዓላዊነቷን ከማስጠበቅ ባለፈ በአፍሪካ እና በአፍሪካ ዳያስፖራ የነጻነት ትግሎች እንዲቀጣጠሉ አድርጓል። በተለይም ከ20ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ ለነበሩ እንቅስቃሴዎች ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ይህ ታሪካዊ ዐሻራ ኢትዮጵያን የጥቁሮች ኩራት፣ ትግል እና ራስን የመቻል ምልክት እንድትሆን አስችሏታል። የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና አዲስ አበባ የአፍሪካ ኅብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ ኢትዮጵያ የአኅጉሪቷ የዲፕሎማሲ ማዕከል ሆና እንድትቀጥል አስችሏል። እ.አ.አ በ1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ኅብረት) ታሪካዊ ምሥረታ የተካሄደው በኢትዮጵያ ነው። ኢትዮጵያ ከድርጅቱ መሥራች ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ይህም የአፍሪካ የጋራ የፖለቲካ ድምጽ እንድትሆን ምክንያት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሴኤ) እና ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ተቋማት የሚገኙባት ኢትዮጵያ፤ በዲፕሎማሲው ምክክር እና ውሳኔ ሰጪነት ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የበለጠ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ድምጽ ኢትዮጵያ በቅኝ አለመገዛቷ ለፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ ሥር መስደድ ወሳኝ ነው። በፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ለአፍሪካ አንድነት እና የጋራ ምላሽ አጥብቃ ስትሞግትም ቆይታለች። በአፍሪካ ኅብረት እና በተለያዩ መድረኮች ኢትዮጵያ የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን መፈታት አለባቸው የሚለውን እሳቤ ለማስረጽ አበክራ እየሠራች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተኮር መፍትሔዎች ከቃላት ባለፈ በአኅጉራዊ የትሥሥር አጀንዳዎች፣ ሰላም እና ደኅንነት ማዕቀፎች እንዲሁም የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ፈተናዎች እንዲፈቱ ድጋፏን በመስጠት ቁርጠኝነቷን አሳይታለች። የአፍሪካ አኅጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነትንም በፍጥነት አጽድቃ ወደ ሥራ ማስገባቷ የዚሁ አንድ ማሳያ ነው። ሰላም ማስከበር እና ቀጣናዊ መረጋጋት ኢትዮጵያ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ስትራቴጂካዊ ሚና እየተወጣች ነው። በዚህም መሠረት ለተባበሩት መንግሥታት እና የአፍሪካ ኅብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማድረግ ከአፍሪካ ሀገራት ቀዳሚውን ድርሻ ትይዛለች።   ሶማሊያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ ግጭት ባለባቸው የአፍሪካ ሀገራት ወታደሮቿን በመላክ ለሰላም እና ደኅንነት ያላትን ሚና በተግባር ገልጣ አሳይታለች። የተባበሩት መንግሥታትም ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር እየተወጣች ላለው ሚና ምሥጋናውን ማቅረቡ ይታወቃል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሀገራት ያሉ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የተወጣችው የእርቅ እና የዲፕሎማሲ ሚናም ተጠቃሽ ነው።   የኢኮኖሚ እድገት እና ቀጣናዊ ትሥሥር ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል በዋናነት ትጠቀሳለች። በ2017 ዓ.ም ማብቂያ የተመረቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በግንባታ ላይ የሚገኘው ኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከግዙፍ መሠረተ ልማትነታቸው ባለፈ ቀጣናዊ ትሥሥር በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሚና አላቸው። ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢነርጂ የስኅበት ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል። ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት የምትሸጠው ኢነርጂ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን የሚያሳልጥ ነው። የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መንገድን ጨምሮ የመንገድ መሠረተ ልማቶች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኢትዮጵያን የቀጣናዊ ትሥሥር ማዕከል እንድትሆን እያደረጓት ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት እየተከናወነ ያለው አረንጓዴ ዐሻራም፤ ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ትብብር እና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተምሳሌት ማድረግ ችሏል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ አጀንዳ የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ትገኛለች። የባህል እና የሥልጣኔ አስተዋጽዖ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ታሪክ፣ ቱባ ባህል እና ብዝኃነት መገለጫዋ ናቸው። የቋንቋ ብዝኃነት በአፍሪካ ውስጥ ገራገር የዲፕሎማሲ ኃይል (Soft Power) እንዲኖራት አስተዋጽዖ አድርጓል። የኢትዮጵያ የሀገርነት ታሪክ እና የሥልጣኔ ትርክት አፍሪካ ያሏትን ጥልቅ የታሪክ ሥሮች ይበልጥ አጉልቶ የሚያሳይ ነው። የኢትዮጵያ ብዝኃ ማንነቶች፣ ሀገር በቀል ዕውቀቶች እና አስደማሚ የሥነ-ሕንጻ ሥራዎች በአፍሪካ ባህል እና ሥልጣኔ ውስጥ ያላቸው ሚና ትልቅ ነው። ኢትዮጵያ አሁንም በአፍሪካ አንድነት እና መረጋጋት ውስጥ እንደ ቁልፍ ምሰሶ ትታያለች። በአኅጉሪቱ ውስጥ ያላት ድርሻ በታሪክ ሥር የሰደደ እና አሁን ባለው ዘመን በዲፕሎማሲ፣ በሰላም ግንባታ እና ልማት ሥራ በግልጽ ጎልቶ ይታያል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የፖለቲካ መዲና እንዲሁም የአይበገሬነት እና የነጻነት ምልክት ናት። አፍሪካ አንድነቷን ለማረጋገጥ፣ የተረጋጋ አኅጉር ለመፍጠር እና በራስ ዐቅም ነገሮችን የመከወን ጉዞ ትልም ውስጥ የኢትዮጵያ ድርሻ ቁልፍ ነው።   39ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ “ዘላቂ የውኃ ኑረትና ንጽህና ሥርዓት፤ ለአጀንዳ 2063 ስኬት” በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬና ነገ በኅብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። ጉባዔው ኢትዮጵያ አኅጉራዊ የፖለቲካ እና ዲፕሎማሲያዊ መድረክ መሆኗን ዳግም የምታሳይበት ነው።
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!!
Feb 6, 2026 343
"ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በያንተስራ ወጋየሁ -ዲላ ቀን ቀንን እየወለደ ጊዜ ሳያቋርጥ እንደ ዥረት መፍሰሱን አያቆምም። ትናንት አዲስ የነበረው አሮጌው የሚባልበት፣ ዛሬ አዲስ ሆኖ ነገ አሮጌ ለመባል ይሮጣል። ወቅቶች ይፈራረቃሉ፣ ይመሻል፣ ይነጋል፣ ትናንት ለዛሬ፣ ዛሬ ለነገ እንዲህ እንዲህ እየተቀባበሉ ዘመን ዘመንን እየተካ ዛሬ ላይ ተደርሷል።   በጥምር ግብርናውና በቡናው የሚታወቀው ጌዴኦ ትናንትን ሸኝቶ ዛሬን እንደ አዲስ ለመቀበል ሽር ጉድ እያለ ነው። በክረምቱ የተዘራው ሰብል ተሰብስቦ ወደ ጎተራ እንዳስገባ ጌዴኦ አዲስ ዓመቱን ‹‹ዳራሮ››ን ይቀበላል። ዳራሮ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ቂም የያዘ ቂምና ቁርሾውን የሚተውበት፣ ወጣቶች የሚተጫጩበት፣ አዛውንቶች ወደ ሽምግልና የሚሸጋገሩበት እሴቶችን በውስጡ የያዘ ነው።   "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው የጌዴኦ አርሶ አደር ካመረተው ምርት ለመሪው፣ ልጆች ለወላጆችና ለአሳዳጊዎቻቸው፣ አዲስ ተጋቢዎች ለአማቾቻቸው፣ ቂም የያዘ ሰው እንዲሁ የተቀየመውን ሰው ይቅርታ ለመጠየቅ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። "ጉማታ" በጌዴኦ ዘመን መለወጫ ወቅት የሚፈጸም ስጦታ ነው። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማኅበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ነው። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። በዳራሮ በዓል አከባበር ውስጥ "ጉማታ" እጅግ አስፈላጊና ትልቅ ትርጉም ያለው ባህላዊ የክብር ስጦታ የመስጠት ሥርዓት ነው። "ጉማታ" ማለት በቀጥታ ትርጉሙ "ስጦታ" ማለት ቢሆንም፣ በጌዴኦ ባህል ግን ከስጦታ በላይ ነው። ምስጋናን፣ ፍቅርን፣ አክብሮትንና በረከትን የመጋራት መገለጫ ነው።   የጌዴአ ባህላዊ የባሌ ስርዓት መሪ ሆነው የሚሰየሙት አባ ገዳ ለህዝብ ከመጸለይ፣ ከማስታረቅና ክፉን በማውገዝ ህዝቡ ተፈጥሮን እንዲንከባከብ ከማስተማር ውጭ አይዘሩም፣ አይነግዱም፣ አልፎም እንሳስትን አያረቡም፡፡ የዳራሮ በዓልን ተከትሎ ህዝቡ የሚያቀርብላቸውን "ጉማታ" በመቀበል ባህላዊ የመሪነት ሚናቸውን በአግባቡ ከመወጣት ውጪ። ኑሮው ከጥምር እርሻ ጋር የተቆራኘው የጌዴኦ ሕዝብ ዘርቶ ካጨደው፣ አርብቶ ካገኘው ከብት፣ አንቦ ከቆረጠው ማር፣ ከሁሉም በአይነት በአይነቱ ሸክፎ ዳራሮ ወደ ሚከበርበት ሶንጎ (አደባባይ) ይተማል። ለጉማታ ከሚቀርቡ ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው ስጦታዎች አንዱ ማር ነው። ማር በጌዴኦ ዘንድ የጣፋጭ ዘመንና የጤና ምልክት ተደርጎ ይወሰዳልና ዋናው ስጦታ ነው። ጌዶኦዎች ቡና፣ ቅቤና ባህላዊ ምግቦች፣ የቁም እንስሳት በግና ስንጋ እንዲሁም ገንዘብ በመያዝ በበዓሉ ውስጥ የጉማታ ስርዓት ሲደርስ ተሽቀዳድመው ለአባ ገዳው በመስጠት ምርቃት ይቀበላሉ።   "ጉማታ" የተቀበለው ሰው የሚመርቀው ምርቃት በሰጪው ሕይወት ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይታመናልና ከስጦታው ይልቅ ምርቃቱ ትልቅ ዋጋ አለው። "ያገኘሁትን ምርት ብቻዬን አልበላም" ብሎ የሚያምነው ጌዴኦ በረከትን ማካፈል ለቀጣዩ ዓመት ተጨማሪ በረከት እንደሚያገኝ ስለሚያውቅ ጉማታ መስጠት የዘመናት ቅርሱ ነው። ጉማታ ከአባ ገዳና ከባህል ሽማግሌዎች ባለፈ አርሶ አደሩ ከማጋኖ (ከፈጣሪ) ያገኘውን በረከት ለሚወዳቸውና ለሚያከብራቸው ሰዎች የሚያቀርብበት መንገድ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ገልጸዋል።   ልጆች ለወላጆቻቸውና ለቤተሰብ አባላት ላሳደጓቸውና ለሰጧቸው ምርቃት ምስጋናቸውን ለመግለጽ ጉማታ ይዘው ይሄዳሉ። በቅርቡ ጋብቻ የመሠረቱ ወጣቶች ወደ አማቾቻቸው ቤት ጉማታ ይዞ በመሄድ ዝምድናቸውን ያጠናክራሉ። በዓመቱ ውስጥ ቅሬታ ወይም ቂም ካለ፣ በዳራሮ ወቅት ጉማታ ይዞ በመሄድ ይቅርታ ይጠየቃል። ጉማታ የሰውን ልብ ለማለስለስና አዲስ ዓመትን በሰላም ለመጀመር ያገለግላል ተብሎ ስለሚታመን። ጉማታ በቤት ውስጥ ተዘጋጅቶ ወደ ታላላቆች ቤት ወይም ወደ ማህበረሰቡ አደባባይ የሚወሰድ በመሆኑ፣ የግለሰብን ደስታ ወደ ማህበረሰባዊ ደስታ የሚቀይር ድልድይ ስለመሆኑም ነው ዋና አስተዳዳሪው የጠቆሙት። በአጠቃላይ ጉማታ ከሌለ የዳራሮ በዓል ሙሉ አይሆንም። ጉማታ የጌዴኦን ሕዝብ አንድነት የሚያጸና፣ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር ሀገር በቀል እሴት ነው። ይህም የመደጋገፍ እሴትን ከማጠናከር በተጓዳኝ ህዝቡ የመንግስት ገቢን እንዲሁም በማህበረሰብ ተሳትፎ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆን መሰረት የጣለ ነው ይላሉ።   የዘንድሮው ዳራሮ ከቤት በተለይም ከአባ ገዳው መኖሪያ አንስቶ በሶንጎዎችና በየደረጃው በሚገኙ መዋቅሮች በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ጭምር እየተከበረ መሆኑን ያነሱት አስተዳዳሪው ጉማታም ዋናው የበዓሉ እሴት ሆኖ እየተከበረ ነው ብለዋል። ባህልና ማንነትን በማስጠበቅና በማዳበር፣ ባህሉ ወደ ወጣቶች እንዲተላለፍ በማበረታታት እንዲሁም የጌዴኦ ባህልን ለሌሎች ህዝቦች ለማስተዋወቅና የማህበረሰብ አንድነትና ባህላዊ እሴትን ለማጠናከር እያገለገለ ያለው የጌዴኦ ዘመን መለወጫ ዳራሮ ጥር 29 እና 30 በዲላ ከተማ ይከበራል። የዳራሮ በዓል የጌዴኦን ሕዝብ የሥራ ባህል፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ዕውቀትና የሰላም እሴት ለዓለም የሚያሳይ ትልቅ አጋጣሚ ነው። ይህ በዓል በተለይ የጌዴኦ የባህላዊ መልክዓ ምድር (Cultural Landscape) በዩኔስኮ (UNESCO) በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ተከትሎ፣ አሁን ላይ ከቤትና ከአደባባይ አልፎ ዓለም አቀፋዊ ትኩረት እያገኘ ያለ ታላቅ እሴት ሆኗል። የዓመት ሰው ይበለን!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም