ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በሴካፋ ዞን ማጣሪያ ታንዛንያ 11 ግቦችን በማስቆጠር ጅቡቲን አሸነፈች
Nov 18, 2025 36
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት ጨዋታ ታንዛንያ ጅቡቲን 11 ለ 0 ረታለች። ማምሻውን በድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሉክማን አሊ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። ኢሳ ቾሌ፣ ሳዳም ሃሚስ፣ ንሂንጎ ጁማ፣ ሶአን አዳም እና ዲስማስ አታናስ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ታንዛንያ በስድስት ነጥብ ምድብ ሁለትን እየመራች ነው። የታንዛንያው ሉክማን አሊ በስድስት ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መምራት ጀምሯል። በዚሁ ምድብ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ዩጋንዳ ሱዳንን 9 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች። ቡድኑ በስድስት ነጥብ በታንዛንያ በግብ ክፍያ ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። የምድቡ ሶስተኛ ጨዋታዎች አርብ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄዱ ሲሆን ታንዛንያ ከዩጋንዳ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ጅቡቲ ከብሩንዲ ሌላኛው የምድቡ መርሃ ግብር ነው። በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዛሬ አራተኛ ቀኑን አስቆጥሯል።
ኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚጨበጥና አይቀሬ መሆኑን ያሳየ ነው
Nov 18, 2025 43
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በመፍጠርና መፍጠን የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚጨበጥና አይቀሬ መሆኑን ያሳየ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መስሪያ ቤት በዚህ ሳምንት መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከእድሜው በላይ የሚጨበጥ ውጤት ማስመዝገብ የቻለ ተቋም ነው፡፡ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በመደመር መንግስት ላይ መፍጠር፣ መፍጠንና በዝላይ ማለፍ የሚሉ ጽንሰ ሀሳቦችን በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ዓለም ከደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የግድ ሁሉንም ሂደት ማለፍ አይጠበቅም ያሉት ኃላፊው፤ ነባራዊውን ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ በዝላይ ማለፍ ይገባል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን የሚያስችላትን አቅም መገንባቷን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የታየው የመፍጠን፣ የመፍጠርና በዝላይ የማለፍ ውጤት የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚጨበጥና አይቀሬ መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በዓለም ላይ ያሉ ሥራዎችን ሁሉ ማከናወን የሚችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሁሉንም ሥራዎች በፍጥነት፣ በጥራትና በግልጸኝነት ማከናወን እንደሚችል ገልጸው፤ ፈጣን ዕድገት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በመዲናዋ ሁሉም ተቋማት ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ነዋሪዎች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚያቀርቡትን ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አቅም መገንባቱን ነው የተናገሩት፡፡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የማያስፈልግበት ቦታ የለም ያሉት ምክትል ከንቲባው፤ የመዲናዋን ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጥና ደህንነት ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በበኩላቸው፤ የከተማ ሥራ በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ ሥራ እና ውሳኔ የሚተላለፍበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ መረጃዎችን ተንትኖ ለቀጣይ የልማት ዕቅዶች ለማዋል፤ እንዲሁም የከተማዋን የክትመት ሁኔታ ለመቆጣጠር ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የተከናወኑ አስደናቂ ሥራዎች መዲናዋን በበቂ የክትመት መረጃ ላይ ተመስርቶ ውሳኔ መስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ በመዲናዋ የሚከናወኑ ህገ ወጥ ግንባታዎችን፣ የመሰረተ ልማት እንቅስቃሴዎችንና ቀጣይ ለመስራት የታቀዱትን በመለየት በቂ መረጃ ይሰጣል ብለዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሳለጠ የመንግስት አገልግሎት በመስጠት የጎላ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመሩን ገልጸው፤ በቀጣይ በሌሎችም ዘርፎች በጋራ መስራት እንዳለብን አይተናል ብለዋል፡፡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ሥራዎችን ቀላል ፈጣንና ግልጽ ማድረግ እንደተቻለ በማንሳት፤ ከተማ አስተዳደሩ የጀመረውን የስማርት ሲቲ ግንባታ ለማላቅ በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በመዲናዋ ዘላቂና ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን በማጎልበት በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ ሥራ ማከናወን ያስችላል ብለዋል፡፡
የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተጀመሩ ስራዎች ውጤት መጥቷል
Nov 18, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦በጉራጌ ዞን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተጀመሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማምጣት መቻሉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ አስታወቁ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ ከመላው ሀገሪቷ የተውጣጡ የጋዜጠኞች ቡድን በጉራጌ ዞን የተካሔዱ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ባለፉት ዓመታት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ ናቸው። ከእነዚህ መካከል በግብርናው ዘርፍ መስኖ እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ መቻሉን ነው የጠቀሱት። በሀገር ደረጃ በተጀመረው የሌማት ትሩፋትም በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እና በአምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉንም አንስተዋል። በመላው ሀገሪቷ በተጀመረው የኮሪደር ልማትም እንዲሁ በገጠርና በከተማ ለኑሮ፣ ለንግድ እና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ከባቢ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል ። የገጠር ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ እንዲቻል በተከናወኑ ተግባራት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የመንገድ ግንባታ መከናወኑንም አብራርተዋል። በዞኑ የሚገኙ የቱሪዝም ጸጋዎችን በማልማት የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለአብነትም በጊቤ ሸለቆ ብሔራዊ ፓርክ ደረጃውን የጠበቀ ሎጅ ለመገንባት እና አካባቢውን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለማልማት እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል።
ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ ነው
Nov 18, 2025 61
ሀዋሳ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በብልፅግና ፓርቲ የሥልጠና መድረክ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ተናገሩ። በአዳማ በተካሄደው የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሥልጠና ላይ የተሳተፉ የሲዳማ ክልል አመራሮች የጋራ የውይይት መድረክ ዛሬ ማምሻውን ተካሄዷል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በፓርቲው የተቀመጡ የትኩረት አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ በክልሉ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ፍጥነትንና ፈጠራን በማከል ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን የበጀት ዓመቱን የሥራ ዕቅድ በመከለስ ውይይት እየተደረገበት እንደሚገኝ ገልጸዋል።፡ በዚህም በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት፣ በግብርናና ገጠር ልማትና በሌሎች የትኩረት መስኮች የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የጋራ ተግባቦት መፍጠር እንደተቻለ ጠቁመዋል፡፡ ይህንን ገቢራዊ ለማድረግም በክልሉ ያሉ የሰላምና ጸጥታና ሌሎች አስቻይ ሁኔታዎችን በመጠቀም እንደሚሰራ ተናግረዋል። ይህንን አጠናክሮ በማስቀጠልም የጊዜ፣ የጉልበትና የበጀት ብክነትን በማስቀረት ባጠረ ጊዜ ውስጥ የተነደፉ ዕቅዶችን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራም አስረድተዋል፡፡ ሰላምና ልማት ወዳዱን ህዝብ እንዲሁም ባለሀብቱን በማስተባበርም የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በተሻለ ሁኔታ እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል። ገቢን አሟጦ በመሰብሰብም የተሻለ የመፈፀም አቅም በመፍጠር ዕቅዶችን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወንም አቅጣጫ መቀመጡን አስታውቀዋል።
መገናኛ ብዙኃን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎችን ማጠናከር አለባቸው
Nov 18, 2025 62
አዲስ አበባ፤ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦መገናኛ ብዙኃን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎች ማጠናከር እንደሚኖርባችው የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ገለጸ። የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የልማት ሥራዎች የነገዋን ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በሚያሳልጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንድትገኝ ያስቻሉ መሆናቸውን የኢዜአ አመራር አባላት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) የሥራ ኃላፊዎችና የሙያተኞች ቡድን አባላትም በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መስሪያ ቤት የቴክኖሎጂ ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ 'ኢንተለጀንስ ለሁሉም' በሚል መሪ ሃሳብ በሁሉም ዘርፍ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ተቋማትም የዕለት ከዕለት ሥራዎቻቸውን በቀላሉ የሚያከናውኑበት ምቹ የቴክኖሎጂ ምኅዳር እየተፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል። የበርካታ ዓለም ሀገራት የመገናኛ ብዙኃንና ሌሎች ተቋማት አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ጥራትና ፍጥነት ያላቸውን ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። መገናኛ ብዙኃን የኢትዮጵያ ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህል የሚያሳድጉበትን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የዘገባ ስራዎችን መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል። ይህም ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የፈጠራ መልካም አጋጣሚዎችን በመጠቀም የሙያተኞችን የሥራ ጫና የሚቀንሱበት ዕድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፤ በበኩላቸው በጉብኝቱ ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ በአፍሪካ ከፍ ያለ ስራ ለመስራት ምን እያከናወነች እንዳለች መመልከታቸውን ተናግረዋል። የኢንስቲትዩቱ ጉብኝታቸውም በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሌሎች መስኮች የኢትዮጵያን የብልጽግና ርዕይ የሚያሳካ ምቹ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መደላድል እየተፈጠረ መሆኑን እንደታዘቡም ገልጸዋል። በኢንስቲትዩቱም ታዳጊዎች የኢትዮጵያን መፃኢ እጣ ፋንታ በተሻለ ጉዞ ማጀብ የሚያስችል የፈጠራ ሥራ እያከናወኑ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ የሚገባን ቴክኖሎጂ ብቻ የመጠቀም ባህል በመቀየር ለአህጉሪቷ ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀስ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ፈጠራ ስራዎች እያከናወነች እንደምትገኝ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል። በጉብኝቱ የተሳተፉ የኢዜአ አመራር አባላትም፤ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካዊያን ጭምር ትምህርት የሚሰጥ አመርቂ ስኬት ማስመዝገቧን እንደታዘቡ ገልጸዋል። በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የፈጠራ ሙያተኛን ለማፍራት የሚከናወኑ ተግባራትም የነገዋን ኢትዮጵያ የተሻለ ማድረግ በሚያስችል የትልም ጉዞ ላይ መሆኗንም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኅዳር 07/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃን መርቀው ስራ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
ፖለቲካ
ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ ነው
Nov 18, 2025 61
ሀዋሳ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በብልፅግና ፓርቲ የሥልጠና መድረክ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ተናገሩ። በአዳማ በተካሄደው የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሥልጠና ላይ የተሳተፉ የሲዳማ ክልል አመራሮች የጋራ የውይይት መድረክ ዛሬ ማምሻውን ተካሄዷል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በፓርቲው የተቀመጡ የትኩረት አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ በክልሉ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ፍጥነትንና ፈጠራን በማከል ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን የበጀት ዓመቱን የሥራ ዕቅድ በመከለስ ውይይት እየተደረገበት እንደሚገኝ ገልጸዋል።፡ በዚህም በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት፣ በግብርናና ገጠር ልማትና በሌሎች የትኩረት መስኮች የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የጋራ ተግባቦት መፍጠር እንደተቻለ ጠቁመዋል፡፡ ይህንን ገቢራዊ ለማድረግም በክልሉ ያሉ የሰላምና ጸጥታና ሌሎች አስቻይ ሁኔታዎችን በመጠቀም እንደሚሰራ ተናግረዋል። ይህንን አጠናክሮ በማስቀጠልም የጊዜ፣ የጉልበትና የበጀት ብክነትን በማስቀረት ባጠረ ጊዜ ውስጥ የተነደፉ ዕቅዶችን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራም አስረድተዋል፡፡ ሰላምና ልማት ወዳዱን ህዝብ እንዲሁም ባለሀብቱን በማስተባበርም የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በተሻለ ሁኔታ እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል። ገቢን አሟጦ በመሰብሰብም የተሻለ የመፈፀም አቅም በመፍጠር ዕቅዶችን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወንም አቅጣጫ መቀመጡን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ያላቸውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ይሰራሉ
Nov 18, 2025 93
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና አዘርባጃን የፓርላማ፣ የህዝብ ለህዝብና የኢንቨስትመንት ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ታገሰ ጫፎ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኤልቺን አሚርባዮቭን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በውይይታቸውም የሁለቱን አገራት ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ህዝብ ለህዝብ ትስስር በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የሁለቱ ሀገራት ፓርላማዎች ትስስር የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ለማጠናከር አጋዥ መሆኑ ተገልጿል። በዚሁ ወቅት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ እንዳሉት፤ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ለረጅም ዓመታት የዘለቀና እየተጠናከረ የመጣ ነው። ሁለቱ ሀገራት ሲቪል ሰርቪሱን ለማጠናከር እንዲሁም በትምህርት ዘርፍ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርጓትን ተግባራት እያከናወነች እንደምትገኝ ጠቅሰው፤ የአዘርባጃን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሰማሩ በጋራ እንሰራለን ብለዋል። አፈ ጉባዔው አዘርባጃን ኮፕ 29ን ማስተናገዷን አንስተው ኢትዮጵያ የኮፕ 32ን በውጤታማነት እንድታስተናግድ አዘርባጃን ያላትን ልምድና ተሞክሮ እንድታጋራ ጠይቀዋል። የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኤልቺን አሚርባዮቭ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ያላቸውን ትስስር የበለጠ ለማጠናከር እንሰራለን ብለዋል። አዘርባጃን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ለዓመታት የዘለቀ ግንኙነት፣ የህዝብ ለህዝብ፣ የባህልና የንግድ ትስስር ለማጠናከር እንደሚሰራ ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማስተናገድ በመመረጧ እንኳን ደስ ያላችሁ ያሉት አምባሳደር ኤልቺን፤ አዘርባጃን ኮፕ 32 በስኬት እንዲጠናቀቅ ሀገራቸው ያላትን ልምድና ተሞክሮ ለማጋራት ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።
የአመራሩን አቅም በመገንባት የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ተግባራት ይከናወናሉ
Nov 18, 2025 64
ሆሳዕና ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአመራሩን አቅም በመገንባት የሕዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያጠናክሩ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተገለጸ። "በመደመር መንግሥት እይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ ለከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተዘጋጀ ሁለተኛው ዙር ስልጠና በሆሳዕና ከተማ መስጠት ተጀምሯል፡፡ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ፓርቲው የአመራሩን አቅም በመገንባት የማሕበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው፡፡ ባለፉት ጊዜያት ለአመራሩ በተሰጡ ስልጠናዎች በክልሉ ዘለቂ እድገት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አንስተዋል፡፡ በሁሉም መስኮች እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን ዘላቂ ለማድረግ አመራሩን የማብቃት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል። በክልሉ የተጀመሩ የለውጡ ትሩፋቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የአመራሩን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም ለማጎልበት ታስቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። አመራሩ ለቀጣይ ዘጠኝ ቀናት የሚሰጠውን ስልጠና በጥብቅ ዲሲፕሊን በመከታተል የሚጠበቅበትን ኃላፊነት መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል፡፡
የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር የኢትዮጵያ ጉብኝት በኢትዮጵያ እና ማሌዢያ መካከል እያደገ ያለውን ወዳጅነት እና ትብብር የሚያሳይ ነው
Nov 18, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018 (ኢዜአ)፦ የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም የኢትዮጵያ ጉብኝት በኢትዮጵያ እና ማሌዢያ መካከል እያደገ ያለውን ወዳጅነት እና ትብብር የሚያሳይ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ለሶስት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ምድረቀደምት ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም ጉብኝት በኢትዮጵያ እና ማሌዢያ መካከል እያደገ ያለውን ወዳጅነት እና ትብብር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ብልጽግና ጉዞ ውስጥም በጠቃሚ ጊዜ የተደረገ ጉብኝት እንደሆነም ተናግረዋል።
ሪፎርሙ የሀገረ መንግሥት ግንባታ አጀንዳ ማሳኪያ መሳሪያ ነው
Nov 18, 2025 118
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ዘመን ተሻጋሪ ተቋማትን በመፍጠር የሀገረ መንግሥት ግንባታ አጀንዳ ማሳኪያ መሳሪያ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ከፈጠረች ከመቶ ዓመታት በላይ ብትሻገርም የዜጎችን ፍትሐዊና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት የማግኘት ፍላጎት ማርካት አልቻለችም፡፡ በዚህም በተለያዩ ጊዜያት የመንግሥት አገልግሎት ሪፎርም ተደርጎ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ከዚህ ግባ የሚባል ውጤት ሳያመጣ ቆይቷል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ለኢዜአ እንዳሉት፤ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ለተቋማት ግልጽ ተልዕኮ የሰጠ ነው፡፡ ሪፎርሙ የዜጎችን የመንግሥት አገልግሎት ፍላጎት በማርካት ዘመን ተሻጋሪ ተቋማት የመፍጠርና የሀገረ መንግስት ግንባታ ተልዕኮን ማሳኪያ መሳሪያ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን አስታውሰው፤ ይሄኛው በስፋት፣ በጥልቀትና ግልጽ ተልዕኮ የተሰጠው መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል፡፡ ለዚህ ኢትዮጵያን የማሻጋር ትልም ስኬት ነፃና ገለልተኛ ተቋማትን በመገንባት መታገዝ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ ሪፎርሙ የአደረጃጀት፣ አሰራርና የቴክኖሎጂ ውስንነቶችን ያርማል ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፃፏቸው መፅሃፎች ላይ ዘላቂ ተቋማትን መገንባት ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸው፤ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣውን ዕዳን ወደ ምንዳ የመቀየር ግብ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሀገረ መንግሥት ግንባታዋን አላጠናቀቀችም ያሉት ሚኒስትሯ፤ ዘመናዊ ተቋማትን ለመገንባት የህግ፣ አሰራርና ሥርዓት መሻሻያ ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በፈጠራና በፍጥነት በመስራት የኢንተርፕረነርሺፕ ተቋማትን በመፍጠር ሂደት ላይ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሯ፤ በሪፎርሙ የተቀመጡ ምሰሶዎችን ገቢራዊ በማድረግ የሰው ሀይላችንን የመፈጸም አቅም አሳድገናል ብለዋል፡፡ ሚኒስቴሩ ተልዕኮውን በብቃት በመወጣት ለሀገራዊ ተልዕኮው የጎላ አበርክቶ እያደረገ መሆኑን በማንሳት፤ ቀልጣፋና ግልጽ አገልግሎት በመስጠት ለሌሎች ልምድ ማካፈል የሚያስችል አቅም መገንባቱን ገልጸዋል፡፡ ሰራተኞችን በማሳተፍ የተቋሙን ችግር የሚፈቱና ተልዕኮዎቹን ለማሳካት የሚያስችሉ ሀሳቦች ያለማቋረጥ የሚመነጩበት ተቋም ሆኗል ብለዋል፡፡ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርሙ ከራሳችን ልጆችና ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት ማሰብ፣ መንደፍ፣ መተግበርና ውጤት ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን የለማውን የኢትዮጵያ ገበያ መረጃ ሥርዓት ከስምንት በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተግባራዊ ለማድረግ መጠየቃቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ ይህ የኢትዮጵያን መቻለ ያረጋግጣል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንተርፕሪነርሺፕ ፕሮግራም ከበርካታ ተቋማት የስልጠና ጥያቄዎች እየቀረበለት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ችግሮች በሀገራዊ ምክክር እንዲፈቱ ድጋፋችንን ይበልጥ እናጠናክራልን -የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Nov 18, 2025 101
አዳማ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፡- የተቃርኖ ሃሳቦችን በማስታረቅ ችግሮች በሀገራዊ ምክክርና ውይይት እንዲፈቱ ድጋፋቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በዓለም ላይ ብዙ ሀገራት ችግሮቻቸውን በውይይት በመፍታትና ቀጣይነት ያለው ለውጥ ማምጣት እንደቻሉ መረጃዎች ያመለክታሉ። ኢትዮጵያም እንዲሁ ችግሮቻን እየፈታች ብትመጣም አሁንም መሻገር ያልተቻሉ ጉዳዮች በመኖራቸው በምክክርና በውይይት መፍታት ያስፈልጋል። ለዚህም ለተቋቋሙ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ስኬታማነት ሁሉም የድርሻውውን መወጣት ይጠበቅበታል። በዚህ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ከተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር ቆይታ አደርጓል። የኩሽ ሕዝቦች ብሔራዊ ንቅናቄ ፕሬዚዳንት አቶ ማንአይቶት በየነ በሰጡት አስተያየት፤ እንደ ፓርቲያችንም ሆነ እንደ ዜጋ ችግሮቻችን መፍታት የምንችለው በምክክር ብቻ እንደሆነ እናምናለንብለዋል። ሀገራዊ ምክክር እንዲደረግ የምክክር ኮሚሽኑ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ድጋፍ በማድረግ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን አውስተዋል። ካልተነጋገርን ችግሮች መፍታት አንችልም ያሉት አቶ ማንአይቶት፤ ሁሉን አካታችና አሳታፊ የሆነ የምክክር በማካሄድና የተቃርኖ ሀሳቦቸን በማስታረቅ ችግሮቻችን በዘላቂነት መፍታት አለብን ነው ያሉት። የሀገራችን ዜጎች፣ ተቋማት፣ ድርጅቶች፣ ማሕበራትና የፖለቲካ ፓርቲዎች ችግሮችን ለመፍታት በውይይት፣ ንግግርና ምክክር አለመግባባቶችን መፍታት ይኖርብናል፤ ለዚህም ድጋፋችንን እናጠናክራለን ሲሉ ገልጸዋል። መንግስት የምክክር ኮሚሽን እንዲቋቋምና ወደ ተግባር እንዲገባ በማድረጉ እናመሰግናለን ያሉት አቶ ማንአይቶት፤ በእስከ አሁኑ ሂደት እስከታችኛው የሕብረተሰብ ክፍል ድረስ በመውረድ ሕዝቡንና ፓርቲውን ይወክላል ያልናቸውን ስምንት አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ አስረክበናል ብለዋል። የጉራጌ አንድነትና ፍትሕ ፓርቲ /ጎጎት/ ሊቀመንበር አቶ ሙሐመድ አብራር በበኩላቸው፤ ችግርችን ከመሰረቱ ለመፍታት ምክክሩ ቁልፍ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ምክክሩ የተቃርኖና የፖለቲካ ፍላጎቶች ዙሪያ የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ ሚና ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ችግሮችና ቅራኔዎችን ለመፍታት በሀገራዊ ምክክሩ የምናገኛቸውን እድሎች መጠቀም አለብን ያሉት አቶ ሙሐመድ፤ ለዚህም የፓርቲያቸው ድጋፍ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በአጀንዳ አሰባሰብ ወስጥ መሳተፋቸውን ያወሱት አቶ ሙሐመድ የምክክር ውጤቱ የተሳካ እንዲሆን በትብብር እንሰራለ፣ ፍፁም ሰላማዊና ሕጋዊ የሆነ የፖለቲካ ትግል ብቻ አማራጫችን መሆን አለበት ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰሞኑን ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር በአዳማ ከተማ ውይይት ማካሄዱ የሚታወስ ነው።
የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር በጋራ መልማትና መስራትን በማንበር ትስስርን አጠናክሯል
Nov 17, 2025 124
ሰመራ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል መከበር በጋራ መልማትና መስራትን በማንበር ትስስርን ማጠናከር መቻሉን የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ አሲያ ከማል ተናገሩ። 20ኛውን የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሐሳብ የአፋርና የአማራ ክልሎች አጎራባች ዞኖች በጋራ በመሆን በአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ አክብረዋል። በዓሉ የተከበረው የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ እና የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ አሲያ ከማልን ጨምሮ የአርጎባ እና ዱለቻ ወረዳ ነዋሪዎች በተገኙበት ነው። የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አሲያ ከማል በዚሁ ወቅት እንደገለፁት የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል መከበር ብሔሮችና ብሔረሰቦች የጋራ የሆኑ እሴቶች እንዲያጠናክሩ እያገዘ ነው። በዓሉ የጋራ እሴቶችን በማጎልበት ክልሎች በአንድ ላይ ሆነው በመስራትና በልማት ግንኙነታቸውን ማጠናከር መቻሉን ተናግረዋል። የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በማጎልበት በአጎራባች ዞኖችና ወረዳዎች ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ዳብሮ በልማታዊ ስራዎች መደጋገፋቸው ተጠናክሯልም ብለዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ በበኩላቸው የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አብሮነትን በማጠናከር ለትብብር የጎላ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። የጋራ ትርክቶችን በማሰረፅ ረገድም በዓሉ ሚናው ከፍተኛ ነው ብለዋል። እጅ ለእጅ ተያይዘን በአንድነት መጓዝ እንደምንችልና የተጋመደውን ወንድማማችነት እና እህትማማችነት በስራና አብሮ በመልማት ማጠናከር ይገባናል ሲሉም ተናግረዋል።
በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 17, 2025 103
ድሬዳዋ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ከሪማ አሊ ተናገሩ። የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች እና አመራሮች 20ኛውን የብሔሮች -ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በፓናል ውይይት አክብረዋል። በመድረኩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈጉባ ከሪማ አሊ፤ የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ስናከብር በየአካባቢው ያልተገለጡ እሴቶችን በማስተዋወቅና በመጋራት እንዲሁም ለሀገር ልማትና ብልጽግና በጋራ በመትጋት መሆን አለበት ብለዋል። ዘንድሮም ለልማት በመትጋትና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት ማክበር እንዳለበት አንስተዋል። በመሆኑም የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫና የፍቅር ምልክት በሆነችው ድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። የድሬዳዋ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ሐይር ሐጂ ኑር፤ የበዓሉ መከበር ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት የተጀመሩ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማሳካት በጋራ ለመትጋት መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸው ለውጤታማነት ቅንና ፍትሃዊ አገልጋይ በመሆን መስራት አለብን ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችም በቅንነትና በታማኝነት ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ለለውጥና ማንሰራራት እንሰራለን ነው ያሉት።
ፖለቲካ
ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ ነው
Nov 18, 2025 61
ሀዋሳ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በብልፅግና ፓርቲ የሥልጠና መድረክ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ተናገሩ። በአዳማ በተካሄደው የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሥልጠና ላይ የተሳተፉ የሲዳማ ክልል አመራሮች የጋራ የውይይት መድረክ ዛሬ ማምሻውን ተካሄዷል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በፓርቲው የተቀመጡ የትኩረት አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ በክልሉ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ፍጥነትንና ፈጠራን በማከል ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን የበጀት ዓመቱን የሥራ ዕቅድ በመከለስ ውይይት እየተደረገበት እንደሚገኝ ገልጸዋል።፡ በዚህም በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት፣ በግብርናና ገጠር ልማትና በሌሎች የትኩረት መስኮች የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የጋራ ተግባቦት መፍጠር እንደተቻለ ጠቁመዋል፡፡ ይህንን ገቢራዊ ለማድረግም በክልሉ ያሉ የሰላምና ጸጥታና ሌሎች አስቻይ ሁኔታዎችን በመጠቀም እንደሚሰራ ተናግረዋል። ይህንን አጠናክሮ በማስቀጠልም የጊዜ፣ የጉልበትና የበጀት ብክነትን በማስቀረት ባጠረ ጊዜ ውስጥ የተነደፉ ዕቅዶችን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራም አስረድተዋል፡፡ ሰላምና ልማት ወዳዱን ህዝብ እንዲሁም ባለሀብቱን በማስተባበርም የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በተሻለ ሁኔታ እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል። ገቢን አሟጦ በመሰብሰብም የተሻለ የመፈፀም አቅም በመፍጠር ዕቅዶችን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወንም አቅጣጫ መቀመጡን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ያላቸውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ይሰራሉ
Nov 18, 2025 93
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና አዘርባጃን የፓርላማ፣ የህዝብ ለህዝብና የኢንቨስትመንት ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ታገሰ ጫፎ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኤልቺን አሚርባዮቭን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በውይይታቸውም የሁለቱን አገራት ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ህዝብ ለህዝብ ትስስር በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የሁለቱ ሀገራት ፓርላማዎች ትስስር የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ለማጠናከር አጋዥ መሆኑ ተገልጿል። በዚሁ ወቅት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ እንዳሉት፤ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ለረጅም ዓመታት የዘለቀና እየተጠናከረ የመጣ ነው። ሁለቱ ሀገራት ሲቪል ሰርቪሱን ለማጠናከር እንዲሁም በትምህርት ዘርፍ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርጓትን ተግባራት እያከናወነች እንደምትገኝ ጠቅሰው፤ የአዘርባጃን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሰማሩ በጋራ እንሰራለን ብለዋል። አፈ ጉባዔው አዘርባጃን ኮፕ 29ን ማስተናገዷን አንስተው ኢትዮጵያ የኮፕ 32ን በውጤታማነት እንድታስተናግድ አዘርባጃን ያላትን ልምድና ተሞክሮ እንድታጋራ ጠይቀዋል። የአዘርባጃን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ኤልቺን አሚርባዮቭ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ያላቸውን ትስስር የበለጠ ለማጠናከር እንሰራለን ብለዋል። አዘርባጃን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ለዓመታት የዘለቀ ግንኙነት፣ የህዝብ ለህዝብ፣ የባህልና የንግድ ትስስር ለማጠናከር እንደሚሰራ ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማስተናገድ በመመረጧ እንኳን ደስ ያላችሁ ያሉት አምባሳደር ኤልቺን፤ አዘርባጃን ኮፕ 32 በስኬት እንዲጠናቀቅ ሀገራቸው ያላትን ልምድና ተሞክሮ ለማጋራት ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።
የአመራሩን አቅም በመገንባት የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ተግባራት ይከናወናሉ
Nov 18, 2025 64
ሆሳዕና ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአመራሩን አቅም በመገንባት የሕዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያጠናክሩ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተገለጸ። "በመደመር መንግሥት እይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ ለከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተዘጋጀ ሁለተኛው ዙር ስልጠና በሆሳዕና ከተማ መስጠት ተጀምሯል፡፡ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ፓርቲው የአመራሩን አቅም በመገንባት የማሕበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው፡፡ ባለፉት ጊዜያት ለአመራሩ በተሰጡ ስልጠናዎች በክልሉ ዘለቂ እድገት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አንስተዋል፡፡ በሁሉም መስኮች እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን ዘላቂ ለማድረግ አመራሩን የማብቃት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል። በክልሉ የተጀመሩ የለውጡ ትሩፋቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የአመራሩን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም ለማጎልበት ታስቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። አመራሩ ለቀጣይ ዘጠኝ ቀናት የሚሰጠውን ስልጠና በጥብቅ ዲሲፕሊን በመከታተል የሚጠበቅበትን ኃላፊነት መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል፡፡
የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር የኢትዮጵያ ጉብኝት በኢትዮጵያ እና ማሌዢያ መካከል እያደገ ያለውን ወዳጅነት እና ትብብር የሚያሳይ ነው
Nov 18, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018 (ኢዜአ)፦ የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም የኢትዮጵያ ጉብኝት በኢትዮጵያ እና ማሌዢያ መካከል እያደገ ያለውን ወዳጅነት እና ትብብር የሚያሳይ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ለሶስት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ወደ ምድረቀደምት ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሴሪ አንዋር ኢብራሂም ጉብኝት በኢትዮጵያ እና ማሌዢያ መካከል እያደገ ያለውን ወዳጅነት እና ትብብር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ብልጽግና ጉዞ ውስጥም በጠቃሚ ጊዜ የተደረገ ጉብኝት እንደሆነም ተናግረዋል።
ሪፎርሙ የሀገረ መንግሥት ግንባታ አጀንዳ ማሳኪያ መሳሪያ ነው
Nov 18, 2025 118
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ዘመን ተሻጋሪ ተቋማትን በመፍጠር የሀገረ መንግሥት ግንባታ አጀንዳ ማሳኪያ መሳሪያ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ፡፡ በኢትዮጵያ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ከፈጠረች ከመቶ ዓመታት በላይ ብትሻገርም የዜጎችን ፍትሐዊና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት የማግኘት ፍላጎት ማርካት አልቻለችም፡፡ በዚህም በተለያዩ ጊዜያት የመንግሥት አገልግሎት ሪፎርም ተደርጎ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ከዚህ ግባ የሚባል ውጤት ሳያመጣ ቆይቷል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ለኢዜአ እንዳሉት፤ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ለተቋማት ግልጽ ተልዕኮ የሰጠ ነው፡፡ ሪፎርሙ የዜጎችን የመንግሥት አገልግሎት ፍላጎት በማርካት ዘመን ተሻጋሪ ተቋማት የመፍጠርና የሀገረ መንግስት ግንባታ ተልዕኮን ማሳኪያ መሳሪያ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን አስታውሰው፤ ይሄኛው በስፋት፣ በጥልቀትና ግልጽ ተልዕኮ የተሰጠው መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል፡፡ ለዚህ ኢትዮጵያን የማሻጋር ትልም ስኬት ነፃና ገለልተኛ ተቋማትን በመገንባት መታገዝ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ ሪፎርሙ የአደረጃጀት፣ አሰራርና የቴክኖሎጂ ውስንነቶችን ያርማል ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፃፏቸው መፅሃፎች ላይ ዘላቂ ተቋማትን መገንባት ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸው፤ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣውን ዕዳን ወደ ምንዳ የመቀየር ግብ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሀገረ መንግሥት ግንባታዋን አላጠናቀቀችም ያሉት ሚኒስትሯ፤ ዘመናዊ ተቋማትን ለመገንባት የህግ፣ አሰራርና ሥርዓት መሻሻያ ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በፈጠራና በፍጥነት በመስራት የኢንተርፕረነርሺፕ ተቋማትን በመፍጠር ሂደት ላይ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሯ፤ በሪፎርሙ የተቀመጡ ምሰሶዎችን ገቢራዊ በማድረግ የሰው ሀይላችንን የመፈጸም አቅም አሳድገናል ብለዋል፡፡ ሚኒስቴሩ ተልዕኮውን በብቃት በመወጣት ለሀገራዊ ተልዕኮው የጎላ አበርክቶ እያደረገ መሆኑን በማንሳት፤ ቀልጣፋና ግልጽ አገልግሎት በመስጠት ለሌሎች ልምድ ማካፈል የሚያስችል አቅም መገንባቱን ገልጸዋል፡፡ ሰራተኞችን በማሳተፍ የተቋሙን ችግር የሚፈቱና ተልዕኮዎቹን ለማሳካት የሚያስችሉ ሀሳቦች ያለማቋረጥ የሚመነጩበት ተቋም ሆኗል ብለዋል፡፡ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርሙ ከራሳችን ልጆችና ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት ማሰብ፣ መንደፍ፣ መተግበርና ውጤት ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን የለማውን የኢትዮጵያ ገበያ መረጃ ሥርዓት ከስምንት በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተግባራዊ ለማድረግ መጠየቃቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ ይህ የኢትዮጵያን መቻለ ያረጋግጣል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንተርፕሪነርሺፕ ፕሮግራም ከበርካታ ተቋማት የስልጠና ጥያቄዎች እየቀረበለት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ችግሮች በሀገራዊ ምክክር እንዲፈቱ ድጋፋችንን ይበልጥ እናጠናክራልን -የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Nov 18, 2025 101
አዳማ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፡- የተቃርኖ ሃሳቦችን በማስታረቅ ችግሮች በሀገራዊ ምክክርና ውይይት እንዲፈቱ ድጋፋቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በዓለም ላይ ብዙ ሀገራት ችግሮቻቸውን በውይይት በመፍታትና ቀጣይነት ያለው ለውጥ ማምጣት እንደቻሉ መረጃዎች ያመለክታሉ። ኢትዮጵያም እንዲሁ ችግሮቻን እየፈታች ብትመጣም አሁንም መሻገር ያልተቻሉ ጉዳዮች በመኖራቸው በምክክርና በውይይት መፍታት ያስፈልጋል። ለዚህም ለተቋቋሙ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ስኬታማነት ሁሉም የድርሻውውን መወጣት ይጠበቅበታል። በዚህ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ከተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር ቆይታ አደርጓል። የኩሽ ሕዝቦች ብሔራዊ ንቅናቄ ፕሬዚዳንት አቶ ማንአይቶት በየነ በሰጡት አስተያየት፤ እንደ ፓርቲያችንም ሆነ እንደ ዜጋ ችግሮቻችን መፍታት የምንችለው በምክክር ብቻ እንደሆነ እናምናለንብለዋል። ሀገራዊ ምክክር እንዲደረግ የምክክር ኮሚሽኑ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ድጋፍ በማድረግ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን አውስተዋል። ካልተነጋገርን ችግሮች መፍታት አንችልም ያሉት አቶ ማንአይቶት፤ ሁሉን አካታችና አሳታፊ የሆነ የምክክር በማካሄድና የተቃርኖ ሀሳቦቸን በማስታረቅ ችግሮቻችን በዘላቂነት መፍታት አለብን ነው ያሉት። የሀገራችን ዜጎች፣ ተቋማት፣ ድርጅቶች፣ ማሕበራትና የፖለቲካ ፓርቲዎች ችግሮችን ለመፍታት በውይይት፣ ንግግርና ምክክር አለመግባባቶችን መፍታት ይኖርብናል፤ ለዚህም ድጋፋችንን እናጠናክራለን ሲሉ ገልጸዋል። መንግስት የምክክር ኮሚሽን እንዲቋቋምና ወደ ተግባር እንዲገባ በማድረጉ እናመሰግናለን ያሉት አቶ ማንአይቶት፤ በእስከ አሁኑ ሂደት እስከታችኛው የሕብረተሰብ ክፍል ድረስ በመውረድ ሕዝቡንና ፓርቲውን ይወክላል ያልናቸውን ስምንት አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ አስረክበናል ብለዋል። የጉራጌ አንድነትና ፍትሕ ፓርቲ /ጎጎት/ ሊቀመንበር አቶ ሙሐመድ አብራር በበኩላቸው፤ ችግርችን ከመሰረቱ ለመፍታት ምክክሩ ቁልፍ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ምክክሩ የተቃርኖና የፖለቲካ ፍላጎቶች ዙሪያ የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ ሚና ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ችግሮችና ቅራኔዎችን ለመፍታት በሀገራዊ ምክክሩ የምናገኛቸውን እድሎች መጠቀም አለብን ያሉት አቶ ሙሐመድ፤ ለዚህም የፓርቲያቸው ድጋፍ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በአጀንዳ አሰባሰብ ወስጥ መሳተፋቸውን ያወሱት አቶ ሙሐመድ የምክክር ውጤቱ የተሳካ እንዲሆን በትብብር እንሰራለ፣ ፍፁም ሰላማዊና ሕጋዊ የሆነ የፖለቲካ ትግል ብቻ አማራጫችን መሆን አለበት ብለዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰሞኑን ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር በአዳማ ከተማ ውይይት ማካሄዱ የሚታወስ ነው።
የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር በጋራ መልማትና መስራትን በማንበር ትስስርን አጠናክሯል
Nov 17, 2025 124
ሰመራ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል መከበር በጋራ መልማትና መስራትን በማንበር ትስስርን ማጠናከር መቻሉን የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ አሲያ ከማል ተናገሩ። 20ኛውን የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሐሳብ የአፋርና የአማራ ክልሎች አጎራባች ዞኖች በጋራ በመሆን በአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ አክብረዋል። በዓሉ የተከበረው የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ እና የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ አሲያ ከማልን ጨምሮ የአርጎባ እና ዱለቻ ወረዳ ነዋሪዎች በተገኙበት ነው። የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አሲያ ከማል በዚሁ ወቅት እንደገለፁት የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል መከበር ብሔሮችና ብሔረሰቦች የጋራ የሆኑ እሴቶች እንዲያጠናክሩ እያገዘ ነው። በዓሉ የጋራ እሴቶችን በማጎልበት ክልሎች በአንድ ላይ ሆነው በመስራትና በልማት ግንኙነታቸውን ማጠናከር መቻሉን ተናግረዋል። የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በማጎልበት በአጎራባች ዞኖችና ወረዳዎች ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ዳብሮ በልማታዊ ስራዎች መደጋገፋቸው ተጠናክሯልም ብለዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ በበኩላቸው የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አብሮነትን በማጠናከር ለትብብር የጎላ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል። የጋራ ትርክቶችን በማሰረፅ ረገድም በዓሉ ሚናው ከፍተኛ ነው ብለዋል። እጅ ለእጅ ተያይዘን በአንድነት መጓዝ እንደምንችልና የተጋመደውን ወንድማማችነት እና እህትማማችነት በስራና አብሮ በመልማት ማጠናከር ይገባናል ሲሉም ተናግረዋል።
በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 17, 2025 103
ድሬዳዋ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ከሪማ አሊ ተናገሩ። የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች እና አመራሮች 20ኛውን የብሔሮች -ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በፓናል ውይይት አክብረዋል። በመድረኩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈጉባ ከሪማ አሊ፤ የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ስናከብር በየአካባቢው ያልተገለጡ እሴቶችን በማስተዋወቅና በመጋራት እንዲሁም ለሀገር ልማትና ብልጽግና በጋራ በመትጋት መሆን አለበት ብለዋል። ዘንድሮም ለልማት በመትጋትና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት ማክበር እንዳለበት አንስተዋል። በመሆኑም የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫና የፍቅር ምልክት በሆነችው ድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። የድሬዳዋ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ሐይር ሐጂ ኑር፤ የበዓሉ መከበር ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት የተጀመሩ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማሳካት በጋራ ለመትጋት መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸው ለውጤታማነት ቅንና ፍትሃዊ አገልጋይ በመሆን መስራት አለብን ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችም በቅንነትና በታማኝነት ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ለለውጥና ማንሰራራት እንሰራለን ነው ያሉት።
ማህበራዊ
በፍትሕ ዘርፉ የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አስችለዋል
Nov 18, 2025 52
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በፍትሕ ዘርፉ የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ለኅብረተሰቡ ምቹና ቀልጣፋ የፍትሕ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ማስቻላቸውን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አለምአንተ አግደው ገለጹ። የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አለምአንተ አግደው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በአገር ደረጃ የፍትሕ ዘርፉን አሠራር ለማሻሻል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው። በፍትሕ ሥርዓቱ የትራንስፎርሜሽን ፕሮጀክቶች ተብለው የተለዩ ከአሥር በላይ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመው፤ ፕሮጀክቶቹ በሁሉም ክልሎች እየተተገበሩ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። የአማራ ክልል ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ በወሰዳቸው እርምጃዎች ሰፋፊ የትራንስፎርሜሽን ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል። በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነፃ የሆነ ዳኝነት ለመስጠት ምቹ መደላደል የሚፈጥሩ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመዋል። የክልሉን ሕዝብ የፍትሕ ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ፣ ጥራት ባለው እና ወጪ ቆጣቢ በሆነ ሁኔታ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል። በተለይም የዜጎችን በግልጽ ችሎት የመዳኘት መብት ለማረጋገጥ ምቹ የሥራ ቦታዎችንና ሁኔታዎችን በመፍጠር ረገድ ውጤታማ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። አገልግሎት አሰጣጡን ተደራሽ ለማድረግ ዜጎች ባሉበት አካባቢ ሆነው አቤቱታ እንዲያቀርቡ፣ ፋይል እንዲከፍቱ እንዲሁም ለመከራከር የሚችሉባቸው የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ከመደበኛው የፍትሕ ሥርዓት በተጨማሪ ዜጎች አማራጭ የክርክር መፍቻ ሥርዓቶችን እንዲጠቀሙ ለማበረታታት በክልሉ የባህል ፍርድ ቤቶችን በማደራጀት ወደ ሥራ ለማስገባት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የዳኝነት አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል የዳኞችን አቅም የመገንባት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው፤ በተለይም የክልሉን የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት እንደገና የማደራጀት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል። የዳኝነት ሥርዓቱን ግልጽ፣ ተጠያቂ፣ ምቹና ተደራሽ ለማድረግ አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ ማገዝ ወሳኝ ተግባር መሆኑን ጠቅሰዋል። እንደ ሀገር ከደረስንበት የዕድገት ደረጃ አኳያ ቴክኖሎጂን መጠቀም ግድ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ በተለይም ለፍርድ ቤቶች ነፃና ገለልተኛ ዳኝነት ለመስጠት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። በፍትሕ ዘርፉ የተጀመሩ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች አገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥ ወሳኝ መሆናቸውን አንስተው፤ የተገልጋዮችን እንግልት ከማስቀረት አኳያ ውጤት ማስገኘታቸውን ተናግረዋል። በተጨማሪም የዳኝነት አገልግሎቱን ይበልጥ ግልጽና ተጠያቂ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ጠቁመዋል።
በክልሉ የተሟላ እውቀትና ስብዕና ያለው ዜጋ ለማፍራት ትኩረት ተሰጥቷል
Nov 18, 2025 55
ቦንጋ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የትምህርት ሥራን ውጤታማነት በማረጋገጥ የተሟላ እውቀትና ስብዕና ያለው ዜጋ ለማፍራት ትኩረት መደረጉን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለፀ። በቦንጋ ከተማ አስተዳደር የተገነባው ሸታ ሞዴል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዛሬ ተመርቋል። በምረቃው ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊና የመማር ማስተማር ዘርፍ ሀላፊ ደስታ ገነሜ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በክልሉ የትምህርት ስራን ውጤታማነት በማረጋገጥ ብቁ ዜጋ ማፍራት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው። የትምህርት ጥራትን ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ በማስጠበቅ ተማሪዎች ከቅድመ መደበኛ ትምህርት ጀምሮ ተገቢውን እውቀትና ክህሎት እንዲይዙ ይሰራል ሲሉ ገልጸዋል። ለዚህም ደረጃቸውን የጠበቁና ግብአት በበቂ ሁኔታ የተሟላላቸው 61 ሞዴል ቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት ዕቅድ ተይዞ ቀድመው የተጠናቀቁት 26ቱ ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ተናግረዋል። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፤ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካው ዘርፍ የሚሰሩ ሥራዎች ውጤታማ ሆነው እንዲቀጥሉ ለትምህርት ጥራት ትኩረት መሰጠት እንዳለበት ገልጸዋል። ታዳጊ ልጆች መልካም ስነምግባርና ተገቢ እውቀት ጨብጠው እንዲያድጉ በዞኑ 17 ሞዴል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን ገልፀዋል። ህፃናት ከታች ጀምሮ በጥሩ ስነምግባርና በእውቀት ተኮትኩተው እንዲያድጉ እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተክለአብ ቡሎ (ዶ/ር) ናቸው። ከዚህ ቀደም የነበረው መማሪያ ክፍል ለሕጻናቱም ሆነ ለመምህራን ምቹ አልነበርም ያሉት መምህርት አበባ ገብሬ ፣ ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤት ችግሩን ከመፍታት ባለፈ የሥራ ተነሳሽነትን ያሳድጋል ብለዋል። በአካባቢያቸው ደረጃውን የጠበቀ ትምህርት ቤት መገንባቱ እሳቸውን ጨምሮ ልጁን በግል ትምህርት ቤት ከፍሎ ማስተማር ለማይችል ወላጅ ትልቅ እፎይታ መሆኑን የገለፁት ደግሞ አቶ መላኩ ማሞ የተባሉ የተማሪ ወላጅ ናቸው።
የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአርሶ አደሮችን የደረሱ ሰብሎች ሰበሰቡ
Nov 18, 2025 49
አክሱም፤ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና የትምህርት ማህበረሰቡ የአርሶ አደሮችን የደረሱ ሰብሎች ሰበሰቡ። በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር በርህ ታፈረ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማሩ ስራ በተጓዳኝ በማህበረሰብ አገልግሎት የነቃ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት በመኸሩ የለማው የአርሶ አደሮች አዝመራ ወቅቱን ባልጠበቀ ዝናብ እንዳይበላሽ ተማሪዎችና አጠቃላይ የትምህርት ማህበረሰቡ በዘመቻ የስብሰባ ስራ አከናውነዋል ብለዋል። በዘመቻውም ከህዳር 07 እስከ ህዳር 09/2018 ዓ.ም በላዓላይና ታሕታይ ማይጨው ወረዳዎች የደረሱ ሰብሎችን መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል። በምርት መሰብሰብ ዘመቻውም በአካልና ጉዳተኞችና በአቅመ ደካማ ወገኖች ማሳ ላይ የደረሰ የሰብል ምርት መሰብሰቡን ገልፀው፤ ዩኒቨርሲቲው በዘመቻው ላይ ለተሳተፉ የከተማ ነዋሪዎችም ነፃ የመጓጓዣ አገልግሎት ማቅረቡን አብራርተዋል። ምርት ከተሰበሰበላቸው አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር አባዲት ገብረስላሴ እና አርሶ አደር አክሊሉ ፍስሃ ፅዮን፤ የደረሰ ሰብላቸው በነፃ የተሰበሰበላቸው በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸዋል። በዚህም ምርቱ ለብልሽት እንዳይዳረግ ከመሰብሰቡ ባሻገር ለጉልበት ሰራተኞች ያወጡት የነበረውን ወጪ ያስቀረላቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰብል መሰብሰብ ዘመቻው ላይ የተገኘው የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ምክትል ፕሬዚዳንት ተማሪ ቴዎድሮስ ለአረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞችና አቅመ ደካማ ወገኖችን ነፃ አገልግሎት በመስጠታችን ተደስተናል ብሏል። በቀጣይም በሌሎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ላይ በንቃት በመሳተፍ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲልም አረጋግጧል።
ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሉ የኩላሊት እጥበት ማሽን ስራ አስጀመረ
Nov 18, 2025 67
ነቀምቴ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ሪፈራል ሆስፒታል ከኦሮሚያ ጤና ቢሮ በድጋፍ ያገኘውን የኩላሊት እጥበት ማሽን ስራ አስጀመረ። ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት እንዳለው የተገለጸው የኩላሊት እጥበት ማሽኑ በዋናነት በምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢ የሚገኙ ታካሚዎችን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ነው የተገለጸው። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ጤና ሳይንስ ኢንስቲትዩት ኤክስኪውቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር መሰረት በለጠ እንዳሉት ማሽኑ በቀን ለአስራ ሁለት ሰው አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ነው። ዛሬ ስራ የጀመረው ማሽን የታካሚውን እንግልት እና ወጪ የሚቀንስ መሆኑንም ተናግረዋል። በሆስፒታሉ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የኩላሊት ሰብስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር ካሳሁን በንቲ፣ በድጋፍ የተገኘው የህክምና ማሽን የሆስፒታሉ ታካሚዎች ፈጣን የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እድልን የፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት አባገዳ አስፋው ከበደ በበኩላቸው፤ ሆስፒታሉ በአዳዲስ የህክምና ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ህብረተሰቡን ለማገልገል መዘጋጀቱ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። የኩላሊት በሽታ የበርካታ ወገኖች የጤና ስጋት በመሆኑ ሆስፒታሉ ለህክምናው የሰጠው ትኩረት የሚደነቅ ነው ያሉት ደግሞ በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት ሼህ ተማም መሀመድ ናቸው። ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ መታከም ለብዙ ወጪ እና እንግልት ይዳርጋል ያሉት ሼህ ተማም ይህ የህክምና አገልግሎት በነቀምቴ ከተማ መጀመሩ ጠቀሜታው ዘርፈ ብዙ መሆኑን አንስተዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቨ ሪፈራል ሆስፒታል አመራሮች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተጀመሩ ስራዎች ውጤት መጥቷል
Nov 18, 2025 58
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦በጉራጌ ዞን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተጀመሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማምጣት መቻሉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ አስታወቁ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ ከመላው ሀገሪቷ የተውጣጡ የጋዜጠኞች ቡድን በጉራጌ ዞን የተካሔዱ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ባለፉት ዓመታት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ ናቸው። ከእነዚህ መካከል በግብርናው ዘርፍ መስኖ እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ መቻሉን ነው የጠቀሱት። በሀገር ደረጃ በተጀመረው የሌማት ትሩፋትም በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እና በአምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉንም አንስተዋል። በመላው ሀገሪቷ በተጀመረው የኮሪደር ልማትም እንዲሁ በገጠርና በከተማ ለኑሮ፣ ለንግድ እና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ከባቢ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል ። የገጠር ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ እንዲቻል በተከናወኑ ተግባራት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የመንገድ ግንባታ መከናወኑንም አብራርተዋል። በዞኑ የሚገኙ የቱሪዝም ጸጋዎችን በማልማት የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለአብነትም በጊቤ ሸለቆ ብሔራዊ ፓርክ ደረጃውን የጠበቀ ሎጅ ለመገንባት እና አካባቢውን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለማልማት እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፋር ሰመራ-ሎጊያ ከተማ የልማት ስራዎችን ይጎበኛሉ
Nov 18, 2025 62
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአፋር ሰመራ-ሎጊያ ከተማ የልማት ስራዎችን ይመለከታሉ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የምድረ ቀደምትነታችን ህያው ምስክርና የሰው ዘር መገኛ፣ የኤርታሌ እሳተ ገሞራና የዳሎል ድንቅ ገፀ ምድር ባለቤት፣ የተፈጥሮና የባህል ሀብታም ወደሆነችው የአፋሮች ውብ ከተማ ሠመራ-ሎጊያ መግባታቸውን ገልጸዋል። በሠመራ ሡልጣን ዓሊሚራህ ሐንፋሬ አውሮፕላን ማረፊያ ደማቅ አቀባበል ላደረጉት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር፣ ለክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ ለሃይማኖት አባቶች፣ ለሀገር ሽማግሌዎች እና ለሠመራ ከተማ ነዋሪዎች ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቆይታቸው በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን እንደሚመለከቱም ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ በፖለቲካ ሴራ አላግባብ ያጣችው የባህር በር በእውነትና በፍትህ ይመለሳል
Nov 18, 2025 45
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በፖለቲካ ሴራ ያጣችው የባህር በር በእውነት እና በፍትህ ይመለሳል ሲሉ የሃይማኖት አባቶች እና አባ ገዳ ገለጹ፡፡ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የየካ ክፍለ ከተማ የሃይማኖት ተቋማት ዋና ሰብሳቢ መልዓከ-ኃይል አባ ኃይለገብርኤል ከተማ ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በሯን ያጣችው እድገቷን እንደ ስጋት በሚመለከቱ ታሪካዊ ጠላቶቿ ሴራ እና በወቅቱ በነበሩ የአገራችን መሪዎች ቸልተኝነት መሆኑንም አንስተዋል። አገሪቱ የባህር በር ማጣቷ በኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጥቅሞቿ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሮ መቆየቱን ጠቅሰው፣ አሁን ላይ መንግሥት ለጉዳዩ የሰጠውን ትኩረት አድንቀዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት እንደነበረች ታሪካዊ ማስረጃዎችን በመጥቀስ፣ የባህር በርን መመለስ የፍትህ ጉዳይ መሆኑንም አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በሴራ ያጣችው የባህር በር በእውነት ይመለሳል፤ የእውነት ጊዜው ደግሞ አሁን ነው ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሼህ መሐመድ ሸሪፍ በበኩላቸው፤ በአሻጥር የሄደውን የባህር በራችንን በሰላም እናስመልሳለን ብለዋል፡፡ የአሁኑ ትውልድ የባህር በርን የማስመለስ አደራ እንደተጣለበት በመረዳት ከመንግሥት ጎን መቆም አለበት በማለት አስገንዝበዋል፡፡ አሰብ የኛ የኢትዮጵያውያን ናት፤ በመሆኑም እኛ የሃይማኖት አባቶች በማስመለስ ሒደቱ ከመንግስት ጎን በመቆም የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ነው ያሉት። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ በርካታ ኢኮኖሚያያዊና ማህበራዊ ለውጦች መመዝገባቸውን ያነሱት ደግሞ አባ ገዳ ወልደአብ ገብረአብ ናቸው፡፡ እነዚህ ለውጦች የተመዘገቡት መንግስትና ህዝብ በጋራ መስራት በመቻላቸው መሆኑን ጠቁመው፤ የባህር በር ለማስመለስ በሚደረገው እንቅስቃሴም እንደ ህዝብ ከመንግስት ጎን እንቆማለን ብለዋል፡፡
በአማራ ክልል አራት የገቢ ግብር አዋጆች ላይ ማሻሻያ ተደረገ
Nov 18, 2025 61
ባሕርዳር፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፡ - በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ ታግዞ ዘመኑን የሚመጥን ግልጽና ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ተግባራዊ ለማድረግ አራት አዋጆች ላይ ማሻሻያ መደረጉ ተገለጸ። በአዋጆቹ ዙሪያ ዛሬ በባሕርዳር ከተማ የምክክር መድረክ ተካሄዷል። የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ አቶ አማረ ሰጤ በመድረኩ ላይ እንዳመለከቱት፤ በክልሉ የታክስ መሰረትን ለማስፋት፣ ፍትሃዊነትንና ገልፅነትን ለማረጋገጥ አዋጆችን ማሻሻል አስፈልጓል። የተሻሻሉትም የክልሉ የገጠር መሬት መጠቀሚያ ክፍያ፣ የግብርና ስራዎችን ግብር ለመወሰን፣ የመንግስት ገቢ ቴምብር ቀረጥ ክፍያ እና የኤክስይዝ ታክስን ጨምሮ አራት አዋጆች መሆናቸውን አንስተዋል። የአዋጆቹ መሻሻልም የሕዝብን ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች በአግባቡ ለመመለስ ገቢ የመሰብሰብ አቅምን ለማስፋትና ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ የታክስ ስርዓት አስተዳደር ለመዘርጋት እንደሚረዳ ገልጸዋል። የተሻሻሉት አዋጆች ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ላይ የቆዩትን በመተካት አሁን ላይ ወቅታዊ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችንና አዳዲስ የገቢ አማራጮችን ለማስፋት በሚያስችል መንገድ የተዘጋጁ መሆኑን አስረድተዋል። አዋጆቹ ከባለድርሻ አካላት የሚነሱ የግብአት ሃሳቦችን በማካተት በቅርቡ በሚካሄደው የክልሉ ምክር ቤት ጉባኤ የሚጸድቁ ይሆናል ብለዋል። አዋጆቹ መሻሻላቸው በቴክኖሎጂ የታገዘና ዘመኑን የሚመጥን የግብር አሰባሰብ ሥርዓት ተግባራዊ የማድረግ ሂደትን የበለጠ የሚያፋጥን ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) ናቸው። እነዚህም የክልሉን የ25 ዓመት አሻጋሪ የእድገትና የዘላቂ ልማት ዕቅድ በአግባቡ ለመፈጸም የሚያስችሉና ተጨማሪ አቅምን የሚፈጥሩ መሆናቸውን አስረድተዋል። የክልሉ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሰላሙ ደረጀ በበኩላቸው፤ አዋጆቹ አዳዲስ የፌዴራል ተሞክሮዎችን በማካተት ፍትሃዊ የግብር አስተዳደር ስርዓትን ለመተግበር እንደሚያስችሉ ተናግረዋል። በመድረኩ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ፣ የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች፣ አርሶ አደሮችና የህግ ምሁራን ተሳትፈዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚጨበጥና አይቀሬ መሆኑን ያሳየ ነው
Nov 18, 2025 43
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በመፍጠርና መፍጠን የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚጨበጥና አይቀሬ መሆኑን ያሳየ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መስሪያ ቤት በዚህ ሳምንት መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከእድሜው በላይ የሚጨበጥ ውጤት ማስመዝገብ የቻለ ተቋም ነው፡፡ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በመደመር መንግስት ላይ መፍጠር፣ መፍጠንና በዝላይ ማለፍ የሚሉ ጽንሰ ሀሳቦችን በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ዓለም ከደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የግድ ሁሉንም ሂደት ማለፍ አይጠበቅም ያሉት ኃላፊው፤ ነባራዊውን ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ በዝላይ ማለፍ ይገባል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን የሚያስችላትን አቅም መገንባቷን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የታየው የመፍጠን፣ የመፍጠርና በዝላይ የማለፍ ውጤት የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚጨበጥና አይቀሬ መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በዓለም ላይ ያሉ ሥራዎችን ሁሉ ማከናወን የሚችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሁሉንም ሥራዎች በፍጥነት፣ በጥራትና በግልጸኝነት ማከናወን እንደሚችል ገልጸው፤ ፈጣን ዕድገት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በመዲናዋ ሁሉም ተቋማት ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ነዋሪዎች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚያቀርቡትን ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አቅም መገንባቱን ነው የተናገሩት፡፡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የማያስፈልግበት ቦታ የለም ያሉት ምክትል ከንቲባው፤ የመዲናዋን ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጥና ደህንነት ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በበኩላቸው፤ የከተማ ሥራ በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ ሥራ እና ውሳኔ የሚተላለፍበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ መረጃዎችን ተንትኖ ለቀጣይ የልማት ዕቅዶች ለማዋል፤ እንዲሁም የከተማዋን የክትመት ሁኔታ ለመቆጣጠር ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የተከናወኑ አስደናቂ ሥራዎች መዲናዋን በበቂ የክትመት መረጃ ላይ ተመስርቶ ውሳኔ መስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ በመዲናዋ የሚከናወኑ ህገ ወጥ ግንባታዎችን፣ የመሰረተ ልማት እንቅስቃሴዎችንና ቀጣይ ለመስራት የታቀዱትን በመለየት በቂ መረጃ ይሰጣል ብለዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሳለጠ የመንግስት አገልግሎት በመስጠት የጎላ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመሩን ገልጸው፤ በቀጣይ በሌሎችም ዘርፎች በጋራ መስራት እንዳለብን አይተናል ብለዋል፡፡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ሥራዎችን ቀላል ፈጣንና ግልጽ ማድረግ እንደተቻለ በማንሳት፤ ከተማ አስተዳደሩ የጀመረውን የስማርት ሲቲ ግንባታ ለማላቅ በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በመዲናዋ ዘላቂና ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን በማጎልበት በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ ሥራ ማከናወን ያስችላል ብለዋል፡፡
መገናኛ ብዙኃን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎችን ማጠናከር አለባቸው
Nov 18, 2025 62
አዲስ አበባ፤ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦መገናኛ ብዙኃን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎች ማጠናከር እንደሚኖርባችው የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ገለጸ። የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የልማት ሥራዎች የነገዋን ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በሚያሳልጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንድትገኝ ያስቻሉ መሆናቸውን የኢዜአ አመራር አባላት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) የሥራ ኃላፊዎችና የሙያተኞች ቡድን አባላትም በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መስሪያ ቤት የቴክኖሎጂ ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ 'ኢንተለጀንስ ለሁሉም' በሚል መሪ ሃሳብ በሁሉም ዘርፍ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ተቋማትም የዕለት ከዕለት ሥራዎቻቸውን በቀላሉ የሚያከናውኑበት ምቹ የቴክኖሎጂ ምኅዳር እየተፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል። የበርካታ ዓለም ሀገራት የመገናኛ ብዙኃንና ሌሎች ተቋማት አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ጥራትና ፍጥነት ያላቸውን ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። መገናኛ ብዙኃን የኢትዮጵያ ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህል የሚያሳድጉበትን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የዘገባ ስራዎችን መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል። ይህም ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የፈጠራ መልካም አጋጣሚዎችን በመጠቀም የሙያተኞችን የሥራ ጫና የሚቀንሱበት ዕድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፤ በበኩላቸው በጉብኝቱ ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ በአፍሪካ ከፍ ያለ ስራ ለመስራት ምን እያከናወነች እንዳለች መመልከታቸውን ተናግረዋል። የኢንስቲትዩቱ ጉብኝታቸውም በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሌሎች መስኮች የኢትዮጵያን የብልጽግና ርዕይ የሚያሳካ ምቹ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መደላድል እየተፈጠረ መሆኑን እንደታዘቡም ገልጸዋል። በኢንስቲትዩቱም ታዳጊዎች የኢትዮጵያን መፃኢ እጣ ፋንታ በተሻለ ጉዞ ማጀብ የሚያስችል የፈጠራ ሥራ እያከናወኑ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ የሚገባን ቴክኖሎጂ ብቻ የመጠቀም ባህል በመቀየር ለአህጉሪቷ ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀስ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ፈጠራ ስራዎች እያከናወነች እንደምትገኝ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል። በጉብኝቱ የተሳተፉ የኢዜአ አመራር አባላትም፤ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካዊያን ጭምር ትምህርት የሚሰጥ አመርቂ ስኬት ማስመዝገቧን እንደታዘቡ ገልጸዋል። በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የፈጠራ ሙያተኛን ለማፍራት የሚከናወኑ ተግባራትም የነገዋን ኢትዮጵያ የተሻለ ማድረግ በሚያስችል የትልም ጉዞ ላይ መሆኗንም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኅዳር 07/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃን መርቀው ስራ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
የአፍሪካን ዘላቂ ብልጽግና ለማረጋገጥ ለክህሎትና ፈጠራ ከፍተኛ ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል
Nov 18, 2025 95
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦የአፍሪካን ዘላቂ ብልጽግና ለማረጋገጥ ምርታማነትን ማሳደግ፣ ለቴክኖሎጂ፣ ለክህሎትና ፈጠራ ከፍተኛ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የግሉ ዘርፍ ልማት፣ ቀጣናዊ ውህደት፣ ንግድ፣ የመሰረተ ልማት፣ ኢንዱስትሪ እና ቴክኖሎጂ ኮሚቴ አራተኛው ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል፡፡ መደበኛ ስብሰባው "ለዘላቂ እና አሳታፊ ዕድገት ቀጣናዊ ውህደትን ለማሳደግ የዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን እና ፈጠራን መጠቀም" በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት ይካሄዳል፡፡ በውይይቱ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችና ፈጠራ የአፍሪካን ቀጣናዊ ትስስርና ዘላቂ ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡ የተመድ ምክትል ዋና ጸሐፊና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክላቨር ጋቴቴ ባደረጉት ንግግር፤ አፍሪካ በአህጉራዊ ውህደትና በፈጠራ ላይ በመመስረት ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን ወደ ዕድል መለወጥ ይገባታል ብለዋል፡፡ ዓለም በፈጣን የቴክኖሎጂ ዑደት፣ የጂኦ-ፖለቲካ ውጥረት እና የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶች ላይ እንደምትገኝ አንስተዋል፡፡ አፍሪካ በርካታ ታዳሽ ኃይሎች ያሏት መሆኑን የገለጹ ሲሆን በቅርቡ ተግባራዊ ያደረገችውን የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ጨምሮ ተወዳዳሪ የማይገኝላቸው ሃብቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ አፍሪካ ፈጠራን በመጠቀም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር እና መድኃኒት የሚያደርሱ ድሮኖችን በመስራት ለፈተናዎቿ ምላሽ መስጠት መጀመሯን በበጎ አንስተዋል፡፡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርታማነትን በዓመት እስከ 40 በመቶ ሊያሳድግ እንደሚችል ጠቅሰው፤ አፍሪካ ይህን ማስፋፋት ይጠበቅባታል ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ለመሰረተ ልማት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ጠቁመው፤ ድንበር ተሻጋሪ የሆነ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአባል ሀገራትና ከአጋሮች ጋር በመተባበር የበለጸገች አፍሪካ ለመገንባት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል፡፡ የግሉ ዘርፍ ልማት፣ ቀጣናዊ ውህደት፣ ንግድ፣ የመሰረተ ልማት፣ ኢንዱስትሪ እና ቴክኖሎጂ ኮሚቴ ሊቀ-መንበር ማማድጃም ዲኒስ ድጃሎ በበኩላቸው፤ አፍሪካ ዘላቂ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ምርታማነትን ማሳደግ፣ በቴክኖሎጂ፣ በክህሎትና በፈጠራ ላይ ማተኮር አለባት ብለዋል፡፡ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እሴትን የሚጨምሩና ተወዳዳሪነትን የሚያሳድጉ በመሆናቸው በስፋት መጠቀም እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለአፍሪካ ዘላቂ ዕድገትና ብልጽግና ምርታማነትን በፈጠራ ማሳደግ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል የዲጂታል ጤና አገልግሎትን የማስፋት ተግባር እየተከናወነ ነው - ቢሮው
Nov 18, 2025 72
አዳማ፤ ህዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የዲጂታል ጤና አገልግሎትን በሁሉም የህክምና ተቋማት በማስፋት ቀልጣፋ ህክምና ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ በግልጽ እንደተመላከተው የመንግስት አገልግሎቶችን በማዘመን የዲጂታል ጤናን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶን ማስፋት አንዱ ተግባር ነው። የጤናውን ዘርፍ አገልግሎት ዲጂታላይዝ ለማድረግ ሲስተሞችን ማበልጸግ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን(ICT) መሰረተ ልማቶችን መዘርጋት፣ የዲጂታል አስተዳደርን ማስፈን እንዲሁም የአሰራር ስርዓት በማዘጋጀት በሀገር አቀፍ ደረጃ መተግበር ዋና ዋና ስራዎች ናቸው። የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ተስፋዬ ክበበው ለኢዜአ እንዳሉት የዲጅታል ጤና ስርዓት የጤና አገልግሎትን ቀልጣፋ፣ ጥራቱን የጠበቀና አስተማማኝ ማድረግ ያስችላል። ለዚህ እውን መሆን በክልሉ በተመረጡ ሆስፒታሎች ከወረቀት ነፃ የሆነው የዲጂታል ጤና አገልግሎት በፓይለት ደረጃ ተተግብሮ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የጤና አገልግሎት አሰጣጡን ግልጽ፣ ተደራሽና ቀልጣፋ ለማድረግ እና እንደ ሀገር ለተጀመረው የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ትልቅ ምዕራፍ እየከፈተ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱን በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ሆስፒታሎች፣ ጤና ጣቢያዎችና ጤና ኬላዎች ደረጃ ለማስፋት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። የቢሾፍቱ አጠቃላይ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ታደሰ ጎንፋ በበኩላቸው ሆስፒታሉ ለሶስት ሚሊዮን ህሙማን አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጸው ሁሉም ዓይነት የህክምና አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ አድርገናል ብለዋል። ይህም የታካሚዎችን እንግልት በመቀነስ ተገልጋዮች በቀላሉ ከሐኪሞቻቸው ጋር እንዲናበቡ በማድረግ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ አድርጓል ነው ያሉት። የዲጂታል ጤና አገልግሎቱ መተግበር ለህሙማን ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲሰጥ ከማድረጉም ባሻገር የተገልጋዮችን እንግልት ቀንሷል ያሉት ደግሞ የጊኒር አጠቃላይ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ኑር ዛላም ናቸው። ዲጂታል ጤና በዘመናዊ አሰራር ለውጥ እያመጡ ካሉ ግንባር ቀደም ዘርፎች መካከል ተጠቃሽ መሆኑንም አመላክተዋል። በአሁኑ ወቅት ሆስፒታሉ ሁለት ሚሊዮን ለሚሆኑ ተገልጋዮች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተናግረው የዲጂታል ጤና ስርዓት መዘርጋቱ አገልግሎቱን ቀልጣፋና ውጤታማ አድርጎታል ብለዋል።
ስፖርት
በሴካፋ ዞን ማጣሪያ ታንዛንያ 11 ግቦችን በማስቆጠር ጅቡቲን አሸነፈች
Nov 18, 2025 36
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት ጨዋታ ታንዛንያ ጅቡቲን 11 ለ 0 ረታለች። ማምሻውን በድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሉክማን አሊ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። ኢሳ ቾሌ፣ ሳዳም ሃሚስ፣ ንሂንጎ ጁማ፣ ሶአን አዳም እና ዲስማስ አታናስ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ታንዛንያ በስድስት ነጥብ ምድብ ሁለትን እየመራች ነው። የታንዛንያው ሉክማን አሊ በስድስት ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መምራት ጀምሯል። በዚሁ ምድብ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ዩጋንዳ ሱዳንን 9 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች። ቡድኑ በስድስት ነጥብ በታንዛንያ በግብ ክፍያ ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። የምድቡ ሶስተኛ ጨዋታዎች አርብ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄዱ ሲሆን ታንዛንያ ከዩጋንዳ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ጅቡቲ ከብሩንዲ ሌላኛው የምድቡ መርሃ ግብር ነው። በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዛሬ አራተኛ ቀኑን አስቆጥሯል።
በሴካፋ ዞን ማጣሪያ ዩጋንዳ ድል ሲቀናት ሶማሊያ እና ኬንያ አቻ ተለያዩ
Nov 18, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ዛሬ እየተደረጉ ይገኛል። በምድብ አንድ በድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ዩጋንዳ ሱዳንን 9 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች። ኦውን ሙኪሳ እና ኤዜ ኮምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል። ቶማስ ኦጌማ፣ ኦዊኖ ጆን በብሪያን፣ ኢስማኤል ፋሃድ፣ ባቢ አብዱልሻኩር እና አርንሎድ ካዬምባ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ዩጋንዳ በስድስት ነጥብ ምድቡን መምራት ጀምራለች። በአንጻሩ ሁለተኛ ሽንፈቷን ያስተናገደችው ሱዳን ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አምስተኛ ደረጃን ይዛለች። የዩጋንዳው ኦውን ሙኪሳ በውድድሩ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ወደ አራት ከፍ በማድረግ የኮከብ ግብ አስቆጣሪነቱን ተመሳሳይ ግቦች ካለው ኢትዮጵያዊው ዳዊት ካሳው ጋር በጋራ እየመሩ ነው። በተያያዘም በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተካሄደ የምድብ አንድ ጨዋታ ሶማሊያ እና ኬንያ አንድ አቻ ተለያይተዋል። አናስ መሐመድ ለሶማሊያ፣ ራይስ ኦቺዬንግ ለኬንያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በዚሁ ምድብ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ አዘጋጇ ኢትዮጵያ ደቡብ ሱዳንን 4 ለ 1 በማሸነፍ በስድስት ነጥብ መሪነቷን አጠናክራለች። በምድብ ሁለት ታንዛንያ ከጅቡቲ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በሴካፋ ዞን ማጣሪያ ኢትዮጵያ ደቡብ ሱዳንን አሸነፈች
Nov 18, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በ16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ የምድብ አንድ ጨዋታ አዘጋጇ ኢትዮጵያ ደቡብ ሱዳንን 4 ለ 1 አሸንፋለች። በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ዳዊት ካሳው ሶስቱን ግቦች በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። ዳዊት በውድድሩ ላይ ሀትሪክ የሰራ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል። እንየው ስለሺ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ፓኖም ጁዎ ለደቡብ ሱዳን ብቸኛውን ጎል በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በተጋጣሚው ላይ ከፍተኛ ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ ነጥቧን ወደ ስድስት ከፍ በማድረግ የምድቡን መሪነት አጠናክሯል። ቡድኑ ቀጣይ ጨዋታውን አርብ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከሶማሊያ ጋር ያደርጋል። ደቡብ ሱዳን በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አምስተኛ ደረጃ ይዛለች። አጥቂው ዳዊት ካሳው በውድድሩ ያስቆጠራቸውን ግቦች ብዛት ወደ አራት ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መምራት ጀምሯል። በምድብ አንድ ሌላኛው መርሃ ግብር ሶማሊያ ከኬንያ ከቀኑ 10 ሰዓት በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ኢትዮጵያ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታዋን ዛሬ ከደቡብ ሱዳን ጋር ታደርጋለች
Nov 18, 2025 77
አዲስ አበባ፤ ህዳር 9/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ዛሬ አራተኛ ቀኑን ይዟል። በዕለቱ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር ከቀኑ 7 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ትጫወታለች። በምድብ አንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ በመጀመሪያ ጨዋታዋ ሩዋንዳን ዳዊት ካሳ እና ሁዜፋ ሻፊ ግቦች 2 ለ 0 አሸንፋለች። ምድቡንም በሶስት ነጥብ እየመራ ይገኛል። በአሜሪካዊው ቤንጃሚን ዚመር የሚመራው ታዳጊ ብሄራዊ ቡድኑ በጨዋታው ላይ ያሳየው ብቃት በብዙዎች አድናቆት አስችሮታል። ተጋጣሚዋ ደቡብ ሱዳን ከሶማሊያ ጋር ባደረገችው የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ሁለት አቻ መለያየቷ ይታወቃል። ኢትዮጵያ የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈች ወደ ግማሽ ፍጻሜ የማለፍ እድሏን ታሰፋለች። በምድብ አንድ ሌላኛው መርሃ ግብር ሶማሊያ ከኬንያ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ይጫወታሉ። ሶማሊያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ከደቡብ ሱዳን ጋር ሁለት አቻ ተለያይታለች። ኬንያ በምድቧ የመጀመሪያ ጨዋታዋን ታደርጋለች። በምድብ ሁለት መርሃ ግብር ሱዳን ከዩጋንዳ በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። ሱዳን በመጀመሪያ ጨዋታዋ በታንዛንያ 6 ለ 0 ስትሸነፍ በአንጻሩ ዩጋንዳ ብሩንዲን 4 ለ 0 አሸንፋለች። በዚሁ ምድብ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ ታንዛንያ ከጅቡቲ በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ታንዛንያ ሱዳንን 6 ለ 0 በመርታት የሴካፋ ማጣሪያን በድል ጀምራለች። ጅቡቲ በምድቧ የመጀመሪያ ጨዋታዋን ታደርጋለች። በሴካፋ ዞን ማጣሪያ 10 ሀገራት በሁለት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ። ማጣሪያው እስከ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። በማጣሪያው ለፍጻሜ የሚያልፉት ሁለት ሀገራት የሴካፋ ዞንን ወክለው ለአፍሪካ ዋንጫ ያልፋሉ። እ.አ.አ በ2026 በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇ ሞሮኮን ጨምሮ 16 ሀገራት ይሳተፋሉ።
አካባቢ ጥበቃ
ባለፈው ክረምት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን እየተንከባከብን ነው - አርሶ አደሮች
Nov 18, 2025 104
አምቦ፤ ህዳር 9/2018(ኢዜአ)፡- ባለፈው ክረምት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን እየተንከባከቡ መሆኑን የምዕራብ ሸዋ ዞን አርሶ አደሮች ተናገሩ። አርሶ አደሮቹ ከዚህ ቀደም በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በተተከሉ ችግኞች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እያገኙ መሆናቸውን ጠቁመው ዘንድሮም በችግኝ እንክብካቤው ላይ አተኩረዋል። ከጨሊያ ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል አስፋው ድንቁ ባለፉት ዓመታት በተከናወነ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የተራቆተ እና የተጎዳ ማሳቸው አገግሞ አሁን ላይ በፊት ከሚያገኙት ምርት በእጥፍ እያገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ቀደም የእርሻ ማሳቸው በጎርፍ ተጠርጎ ምርታማነቱ በመቀነሱ ስጋት ውስጥ ገብተው እንደነበረም አስታውሰዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ በተከታታይ በተተከሉ ችግኞች የአፈር መሸርሸር በመቀነሱ የእርሻ ማሳቸው ምርታማነቱ መጨመሩን አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት የተለያዩ የጥራጥሬ ሰብሎችን እያለሙ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው የተተከሉ ችግኞች የመሬቱን ለምነት የሚጠብቁ በመሆኑ ለከብቶቻቸው መኖ ማግኘታቸውንና አካባቢያቸውም መልካም ገጽፅታ መላበሱን አውስተዋል። ሌላው አርሶ አደር ፋይሳ ቀነኒ በበኩላቸው፣ በአካባቢያቸው የተጎዳ መሬት በአረንጓዴ ዐሻራ ልማት እንዲያገግም በመደረጉ ከዚህ ቀደም ከሚያለሙት የጥራጥሬ ሰብሎች በተጨማሪ ጥምር ጥቅም የሚሰጡ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን አንስተዋል፡፡ መርሃ ግብሩ ከመጀመሩ በፊት ዝናብ ወቅቱን ጠብቆ ስለማይዘንብ ብዙ መቸገራቸውን አስታውሰው አሁን ላይ ግን ዝናቡም ወቅቱን ጠብቆ በመዝነቡ ምርታማነታቸው ጨምሮ የተሻለ ገቢ እያገኙ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ የአካባቢያቸውን ማህበረሰብ በማስተባበር የእርከን ስራ ላይ የአፈር ለምነት እንዲጠብቅና የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ ለተከታታይ ዓመታት በሰሩት ስራ ለውጥ መመዝገቡን ተናግረዋል። የጨሊያ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርናና መሬት አስተዳዳር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢነዑ ተሾመ በበኩላቸው፤ በወረዳው በሚከናወነው የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ስራ የህብረተሰቡ ተሳትፎ እያደገ መጥቷል ብለዋል፡፡ በወረዳው በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ለተተከሉት ችግኞች አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በወረዳው የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ከተጀመረ ወዲህ የአካባቢው ስነ ምህዳር ከመቀየሩም በላይ የአርሶ አደሮቹ ምርትና ምርታማነት መጨመሩን አመልክተዋል። በወረዳው በአረንጓዴ ዐሻራ ልማት መርሃ ግብር ከሃገር በቀል የዛፍ ችግኞች በተጨማሪ ለምግብነት የሚውሉ ማንጐ፣ ሙዝ፣ አቮካዶ እና ቡና ጭምር መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡
ሰውና ተፈጥሮ የተዋደዱበት ቆጠር ገድራ ጥብቅ ደን
Nov 18, 2025 72
ሰውና ተፈጥሮ የተዋደዱበት ቆጠር ገድራ በጉራጌ ዞን ከሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች መካከል አንዱ ነው። ጥብቅ ደኑ ከጉራጌ ዞን ከወልቂጤ ከተማ በ42 ኪሎ ሜትር ርቀት በስተምሥራቅ በእዣ ወረዳ ቆጠር ገድራ ቀበሌ ይገኛል። ጥብቅ ደኑ በበርካታ ሀገር በቀል ዛፎች የተሸፈነ፣ ሰውና ተፈጥሮ የተዋደዱበት፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ የህይወት እስትንፋስ ነው። የቆጠር ገድራ ጥብቅ ደን ቀልብን የሚስብ፣ ነፍስ በሀሴት የምትሞላበት፣ መንፈስ የሚታደስበት ውብ ስፍራ ነው። ቆጠር ገድራ ተዳፋታማ በሆነ ስፍራ የሚገኝ ሲሆን ብዛት ባላቸው ሀገር በቀል ዛፎች ማለትም ዝግባ፣ የኮሶ ዛፍ፣ የሀበሻ ፅድ የተሞላ ነው፡፡ የቆጠር ገድራ የተፈጥሮ ደን ለረጅም ዘመናት ከሰው ንክኪ ተጠብቆ የቆየው በአካባቢው ኅብረተሰብ ነባር ባህል መሠረት የጥንት አባቶች ደኑ እንዳይቆረጥ በቃል ኪዳን/ጉርዳ/ ስለተሳሰሩ መሆኑም ተገልጿል፡፡ 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተውጣጣ የጋዜጠኞች ቡድን በጉራጌ ዞን ከሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎች አንዱ የሆነውን የቆጠር ገድራ ጥብቅ ደንን ጎብኝቷል። የእዣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዘውዱ ዱላ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት ከጥንት ጀምሮ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ደን መቁረጥ እንደ ወንጀል የሚቆጠር፤ በአካባቢው ባህል የሚያስቀጣ ነውር ተግባር ነው፡፡ ጥብቅ ደኑ ከ350 ሄክታር መሬት በላይ እንደሚሸፍን እና በውስጡ ከ18 በላይ የዛፍ ዝርያዎች እንደሚገኙም አንስተዋል። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ መሰረት አመርጋ በበኩላቸው የጉራጌ ህዝብ በስራ ወዳድነቱና ታታሪነቱ የሚታወቅ ከተፈጥሮ ጋር ትልቅ ቁርኝት ያለው መሆኑን ተናግረዋል። በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የሚገኘው የቆጠር ገድራ ጥብቅ የተፈጥሮ ደን ከ700 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠረ የሚነገርለት ሲሆን ህብረተሰቡ ደኑን ጠብቆ ያቆየበት መንገድ ከተፈጥሮ ጋር ላለው ቁርኝት አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። ደኑን በዘላቂነት ጠብቆ በማቆየት አካባቢውን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግናና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑንም ተናግረዋል። ቆጠር ገድራ ጥብቅ ደን በውስጡ ከያዛቸው የዛፍ ዝርያዎች ባለፈ የበርካታ ብዝኃ ህይወት መኖሪያ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የእዣ ወረዳ ደን እና አካባቢ ጥበቃ ልማት ጽህፈት ቤት የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ሂደት አስተባባሪ ብርሃኑ ብርሼ ናቸው። እንደዚህ ዓይነት ጥብቅ ደኖች ሥነ ምሕዳርን በመጠበቅ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ችግሮችን ለመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ብለዋል።
ኢትዮጵያ (ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃ ላላት ጽኑ ቁርጠኝነት እውቅና የሰጠ ነው - ኢጋድ
Nov 15, 2025 106
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃና አረንጓዴ ልማት ቁርጠኝነቷ እውቅና የሰጠ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ገለጸ። የድርጅቱ ዋና ጸሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ኮፕ 32 እንድታዘጋጅ መመረጧን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤውን ማዘጋጀቷ በአየር ንብረት እና ልማት ያላት መሪነት እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። የአካባቢ ስነ ምህዳርን ወደ ነበረበት የመመለስ፣ ዘላቂ እድገትና የማይበገር አቅም ለመገንባት ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያመላክትና ለዚህም ስራዋ እውቅና የሰጠ መሆኑን አመልክተዋል። አረንጓዴ ዐሻራ እና የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት ስራ ማሳያዎች እንደሆኑም ነው የተናገሩት። ኮፕ 32 ለኢጋድ ቀጣና ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጸው ተቋሙ ድርቅ፣ የአየር ንብረት ለውጥ የፈጠረው የዜጎች መፈናቀልና የውሃ እጥረትን ጨምሮ ሌሎች አንገብጋቢ አጀንዳዎች የበለጠ ትኩረት እንዲሰጣቸው እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ኢጋድ ከኢትዮጵያ፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ማዕቀፍ ጽህፈት ቤት(UNFCCC Secretariat) እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን ጉባኤው ሁሉን አሳታፊ፣ የአፍሪካ የቅድሚያ ትኩረቶች ማዕከል ያደረገና ለአየር ንብረት ለውጥ ዘላቂ መፍትሄ የሚገኝበት እንዲሆን በትብብር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። በብራዚል ቤለም እየተካሄደ የሚገኘው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 30) ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን ኮፕ 32 ጉባኤ እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል። የአፍሪካ ሀገራት ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ሙሉ ይሁንታቸውን ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ታሪካዊ ነው - የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር
Nov 15, 2025 114
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 32)ን እንድታስተናግድ መመረጧ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ታሪካዊ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀ መንበሩ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ32)ን እንድታስተናግድ በመመረጧ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጉባኤውን የማስተናገድ ውሳኔው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ታሪካዊ መሆኑን ሊቀመንበሩ ገልጸው ይህም አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃ ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አማካኝነት እያሳየች ያለውን የአየር ንብረት የመሪነት ሚናም አድንቀዋል። ኢትዮጵያ መጠነ ሰፊ የደን መልሶ ልማት እና አረንጓዴ ዐሻራን ጨምሮ ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃ እርምጃዎችን እየወሰደች እንደምትገኝ አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በስኬት በማስተናገድ እምቅ አቅም እንዳላት አንስተው ከፍተኛ ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ጉባኤዎችን ለማዘጋጀት ጠንካራ ተቋማዊ አቅም እና ልምድ አላት ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ ጉባኤውን እንድታስተናግድ መመረጧ በዓለም አቀፍ ትብብር ያላትን ማዕከላዊ ሚና የበለጠ እንደሚያሳድገውም ገልጸዋል። ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ማዕቀፍ(UNFCCC) እና አጋሮች ጋር በመሆን(ኮፕ 32) ሁሉን አካታችና ውጤታማ በማድረግ የአፍሪካን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የበለጠ ለማራመድና ዓለም አቀፍ አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ህብረቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። በብራዚል ቤለም እየተካሄደ የሚገኘው 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ(ኮፕ 30) ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚከናወነውን ኮፕ 32 እንድታስተናግድ ተመርጣለች። የአፍሪካ ሀገራት ለኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ሙሉ ድጋፋቸውን መስጠታቸው ይታወሳል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 481
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 629
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል። ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
Oct 31, 2025 518
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው
Oct 24, 2025 769
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡ ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡ በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 125
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 306
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው። በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው። የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው። “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል። በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 374
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 546
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2095
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2340
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3224
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3313
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 1362
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 922
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6758
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5235
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
በጥምር ግብርና ስኬት ያስመዘገቡት አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ
Nov 14, 2025 245
(በእንዳልካቸው ደሳለኝ - ከወልቂጤ ኢዜአ ቅርንጫፍ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ጨዛ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ለዘመናት ባከናወኑት የግብርና ልማት ሥራ ኑሯቸው ከእጅ ወደ አፍ የዘለለ አልነበረም። ዛሬ ላይ ሆነው ያን ዘመንና ያሳለፉትን ዕድሜ ሲያስታውሱ ይቆጫሉ። በኋላ ቀር መንገድ ሲያከናውኑት ከነበረው የግብርና ልማት ሥራቸው ተጠቃሚ መሆንም፤ ሀብት ማፍራትም ሳይችሉ ቀርተዋል። አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ይባላሉ። ከሰበሰቡት ሰብል ጎተራቸው ሳይጎድል፣ ከእንስሳት እርባታ ስራቸውም ጥገታቸው ሳትነጥፍ ማየት የዘውትር ህልማቸው ነበር። ለም መሬት ይዘው ምርታማ ባለመሆናቸው ሲቸገሩ፣ የሚሰራ ጉልበት ይዘው ማዕዳቸው እየጎደለ የጎልማሳነት ዕድሜ መባቻ ድረስ ችግር ሲፈራረቅባቸው ዓመታትን አሳልፈዋል። ይህ ፍላጎታቸው ሰምሮ፣ ጓሯቸው ለምቶ፣ ቤታቸው ሞልቶና ጥሪት አፍርተው የማየት ውጥናቸው ሳይሳካ ዓመታት ቢቆጠሩም ዛሬ ግን በጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ነገሮች ተቀይረዋል። የዓመታት ምኞታቸውን ማሳካት ጀምረዋል። ከስድስት ዓመታት በፊት በትንሽ መሬት ላይ የጀመሩት የጥምር ግብርና ሥራ ለስኬት እንዲበቁ ከማድረግ ባለፈ በአካባቢያቸው አርአያ የሆኑ አርሶ አደር አድርጓቸዋል። የጥምር ግብርና ስራቸው ለዓመታት ከነበሩበት ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ በማውጣት ለአፍም ለኪስም ሆኗቸዋል። የመንግስት የልማት ትኩረት የሆነው ጥምር ግብርና በውስን መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅንጅት እንዲያለሙ እድል ፍጥሮላቸዋል። በዋናነት በሰብል፣ በእንሰት፣ በፍራፍሬና በእንስሳት እርባታ ላይ አተኩረው እየሰሩ ይገኛሉ። ይህም የአንዱ ክፍተት በሌላው እየተሞለ ውጤታማ ስላደረጋቸው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ ነው። ለቤት ፍጆታ ብቻ ያመርቱ የነበረው የእንሰት ምርትን በማስፋፋት ችግኙንና ተረፈ ምርቱን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጭምር ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያመርቱት ገብስ ለሌሎች አርሶ አደሮች ምሳሌ መሆን ችለዋል። ዝርያቸው የተሻሻሉ ላሞችን ስለሚያረቡም ወተት ከማጀታቸው አይጠፋም። በጓሯቸው የሚያለሙትን አትክልትና ፍራፍሬ ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ፈጥረዋል። አርሶ አደሩ ከንብ ማነብ ሥራቸውም እንዲሁ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው። ከአካባቢው ስነምህዳር ምክንያት ብዙም ያልተለመደውን ቡና በመትከል ለፍሬ አብቅተዋል። የእሳቸውን ፈለግ የተከተሉ ሌሎች አርሶ አደሮችም ቡና ማልማት ጀምረዋል። በእጅ ያለን ሀብት ወደ ውጤት ለመቀየር ተግቶ መስራትና ጽናት ያስፈለጋል ያሉት አርሶ አደር ወልዴ፣ በግብርና ባለሙያዎች የተደረገላቸው ሙያዊ ድጋፍና የተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ለውጤታቸው ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የእርሻ ልማትና የእንስሳት እርባታውን በቅንጅት ማከናወናቸውም እንዲሁ። አርሶ አደር ወልዴ የዓመታት ቁጭታቸው ዛሬ መፍትሄ እያገኘ ነው። የጥምር ግብርና ሥራቸው በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉና ልጆቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እንዲያሳድጉ አስችሏቸዋል። መኖሪያ ቤትን ጨምሮ የተለያየ ሀብት ለማፍራት ምክንያት በመሆኑም ልማቱን አስፋፍቶ ለማከናወን አቅደዋል። አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ጭምር አርአያ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የጉመር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙራዱ ብሩ ናቸው። ቀደም ሲል በገብስ ምርት ላይ ብቻ አተኩረው ይሰሩ የነበረውን የግብርና ሥራ እንዲቀይሩ ምክንያት እንደሆኗቸው ይገልጻሉ። ከአርሶ አደር ወልዴ በወሰዱት ልምድ ወደ ጥምር ግብርና ገብተዋል። በዚህም ድርቅ የመቋቋም አቅም ያለውን እንሰት በማሳቸው በስፋት ማልማት ጀምረዋል። የነበሯቸውን ሀገረሰብ የዳልጋ ከብቶች በተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች በመቀየር የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን ተግተው እየሰሩ ነው። ጥምር ግብርና የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ከአርሶ አደር ወልዴ ተምሪያለሁ ይላሉ። ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባለፈ የመሬት ለምነትን ለማስጠበቅም ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ የጀመርነውን ሥራ እናጠናክራለን ሲሉም ነው የገለጹት። የሙህር አክሊል ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ መኑር ጀማል በበኩላቸው "አርሶ አደር ወልዴ አርጋኒ በውስን መሬት ገብስ፣ እንሰት፣ ቡና እና የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በጥምር በማልማት የራሳቸውን ህይወት ከመቀየር ባለፈ ለሌሎች አርሶ አደሮች አርአያ እየሆኑን ነው ብለዋል። አርሶ አደሩ በሽታ መቋቋም የሚችሉና ለመድሃኒትነት የሚፈለጉ የእንሰት ዝርያዎችን በማፍላት ለገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ። ከዚህም ባለፈ በመጥፋት ላይ የነበሩ የእንሰት ዝርያዎችን የመታደግና የአፈር ለምነት እንዲጠበቅ ጉልህ ሚና ማበርከታቸውንም ተናግረዋል፡፡ የጥምር ግብርና አሰራር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ በመሆኑ በወረዳው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት። የአርሶ አደር ወልዴ ልምድን በማስፋት የሌሎች አርሶ አደሮችም ጓዳ ሞልቶ እንዲትረፈረፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይ በጥምር ግብርና አርሶ አደሩ ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ጭምር እንዲተርፍ የማድርጉ ሥራ ይጠናከራል ብለዋል። ልማቱ እርስ በእርስ የሚደጋገፉና በአንድ መሬት ላይ የተለያዩ ምርቶችን በማግኘት የተሻለ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ግብርናን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚሰራው ሥራ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ በጥቂት መሬት ብዙ ማምረት መቻል ነው። በመሆኑም በተለይ የመሬት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በሥራ ውጤታማ ለመሆን ሁሉም ነገር ምቹና አልጋ በአልጋ መሆን የግድ እንዳልሆነ አርሶ አደሩ ጥሩ ማሳያ ናቸው። ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ዕድል እንዴት ወደሀብትነት መቀየር እችላለሁ ብለው ከሰሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ የእሳቸው የስኬት ጉዞ በቂ ማሳያ ነው። ሰርቶ ለመለወጥም ሆነ ሀብት ለማፍራት ችግሮችን በጽናት ማለፍ እና የሥራ ትጋት ወሳኝ ነውና ተሞክሯቸውን ማስፋት ያስፈልጋል።
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ"
Nov 12, 2025 321
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ" ብርሃኑ ፍቃዱ -ከሰቆጣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልካዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረት ያለው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ማብራራታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ የባህር በሯን ያጣችበትን የ30 ዓመታት ታሪክ ለመቀልበስ ይህን ያህል ዓመት እንደማይወስድ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ ሕጋዊና ተቋማዊ መሰረት የሌለው የሚያስቆጭ ብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል ስለመሆኑም አንስተዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ እና አቶ አድማሱ ደሳለኝ፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር የተወለዱበት ስፍራ፣ የኖሩበት ቀዬ፣ ያሳደጋቸው ማህበረሰብ ... የዘመናት ትዝታና ትውስታቸው እንደሆነ ይገልጻሉ። ይህን የታሪካቸው አካል የሆነውን የባሕር በር ማጣትም የሁል ጊዜ ፀፀትና እንደ ሰውነት ጥላ አብሮዋቸው የሚዞር እውነታ ነው። ከአካባቢው ርቆ ለሚገኝ ሰው ትውስታውን ሲያወራ ለሌላው ተረት ተረት፤ ለራስ ደግሞ የውስጥ ቁስል ማገርሸት ሆኖ ነው የሚሰማው ይላሉ። ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብንና የቀይ ባህር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሸፍጥ ማጣቷ በቀይ ባህር ላይ እየዋኙ፣ ውሃ እየተራጩ፣ በዳርቻው ነፋሻማ ስፍራ እየተዝናኑ... ለኖሩት ለእነ መለሰ እና አድማሱ መቼም የማይረሳ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ለአለም ማሕበረሰብ ጥያቄውን ሲያሳውቁ ተደብቆ ለቆየው ትውስታቸው አዲስ ተስፋ እንደሰጣቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ በአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል ለ12 ዓመታት እንዳገለገሉ በትውስታና ቁጭታቸውን ወደ ኋላ ተመልሰው ያወሳሉ። አሁን በሰቆጣ ከተማ የሚኖሩት አቶ መለሰ ይሄይስ ፤ የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ተደማሪ አቅም ነበር በወቅቱ ይላሉ። ይህን የአሰብ ወደብንና የቀይ ባሕር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሴራ ኢትዮጵያ ስታጣ ይሰሩበት ከነበረው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ስራ አቁመው ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሰቆጣ መምጣታቸውን አውስተዋል። በራሳቸው ላይ ከደረሰባቸው የስራ እና ሃብትና ንብረት ማጣት ፣ እንግልትና ሌሎች ችግሮች በላይ ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተነጠለችበትን ሁኔታ ሲያስቡና ሲያሰላስሉ እንደሚያስቆጫቸው ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን በማጣት የባሕር በር ብቻ ሳይሆን የገቢና ወጭ ንግድን፣ የነዳጅ ማጣሪያ ጭምር ነው ያጣችው ያሉት አቶ መለሰ፤ አሁን ጥያቄው መነሳቱ ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ ገናናነቷ ለመመለስ ያለመ አበረታች ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። መንግስት ያነሳው የባሕር በር ጥያቄም የዘመናት ቁጭታችንን፣ ብስጭታችንን እና ህልማችንን ከተደበቀ ትውስታ፤ ወደ አዲስ ተስፋ የወሰደ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ህጋዊና ታሪካዊ ነው ያሉት አቶ መለሰ ፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝም ለአዲሱ ትውልድ በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። ከ1973 ዓ.ም ጀምረው ለአስር ተከታታይ ዓመታት በአሰብ ወደብ የሲቪል መሃንዲስ ክፍል ሰራተኛ እንደነበሩ ያወሱት አቶ አድማሱ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የባሕር ባር ባለቤት በሆነችባቸው ዘመናት ገናና እና የተከበረች ሀገር ሆና መቆየቷን አንስተዋል። የባሕር በሩ የኢትዮጵያ የገቢና ወጭ ንግድ የሚሳለጥበት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሄን ታላቅ ትሩፋትና ፀጋ ለማስመለስ የተጀመረው እንቅስቃሴ ቁጭትና ትውስታችንን ወደ አዲስ ተስፋ የቀየረ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪካዊ ጠላቶችና ባንዳዎች እኩይ ሴራ የባሕር በር ካጣች ወዲህ ጥያቄውን ማንሳት የማይቻልበት የአፈናው ዘመን አክትሞ በለውጡ መንግስት መነሳቱ አበረታችና ለማስመለስም ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። እኔም ባለኝ አቅም ሁሉ ስለባሕር ባር አስፈላጊነት፣ ጥቅምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ለስኬታማነቱ የድርሻዬ እወጣለሁ ሲሉም ገልጸዋል።