አርእስተ ዜና
ዩኒቨርሲቲዎች አገር በቀል እውቀቶችን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማስተሳሰር ለአገር ግንባታ ማዋል እንዳለባቸው ተገለጸ
Jun 1, 2023 52
ደብረ ብርሃን ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገር በቀል እውቀቶችን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማስተሳሰር ለአገር ኢኮኖሚ ግንባታ እና ለችግሮች መፍቻ ማዋል እንደሚገባ ተጠቆመ። በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ "የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሳምንት ቀን" በተለያዩ ዝግጅቶች በመከበር ላይ ነው። የኢትዮጵያ ባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ካሳሁን ተስፋዬ እንዳሉት፣ የአገር ኢኮኖሚን ለመገንባት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በምርምር የታገዘ ድጋፍ ማድረግ አለባቸው። ተቋማቸው የአገር ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ እንዲቀመጥ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በምርምር እንዲወጡና ለተጠቃሚዎች እንዲደርሱ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በሲዳማ ክልል ይርጋለም ከተማ የቡና ገለባን ወደ ማዳበሪያ ለመቀየር ያከናወነው ስራ ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ ቴክኖሎጂውን ለአርሶ አደሮች እንዲሸጋጋር መደረጉን ተናግረዋል። እንዲሁም የቲማቲም በሽታን በመከላከል የዘርፉን ምርታማት ለማሳደግ ከኬሚካል ነጻ የሆነ የተባይ መከላከያ መድሀኒት ተቋሙ በምርምር ማውጣቱን ነው የገለጹት። ከእዚህ በተጨማሪ የማሽላ ጥንቅሽ ዝርያን ለፋርማሲዩቲካልና ለምግብነት አገልግሎት ለማዋል ከመልካሳ ግብርና ምርምር ጋር ውጤታማ ስራ መሰራቱን ነው ዶክተር ካሳሁን የተናገሩት። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገር በቀል እውቀቶችን ከመጠበቅ ባለፈ ከአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማስተሳሰር አገራዊ ችግሮችን ለመፍታትና ለኢኮኖሚ ግንባታ ማዋል እንዳለባቸው አሳስበው ተቋሙ ለዚሁ ስራ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ጥናትና ምርምር የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር አዝመራ አየሁ በበኩላቸው፣ በዩኒቨርሲቲው ችግር ፈች የምርምር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።   ለዚህም በግብርናው ዘርፍ የተቀናጀ የአሳ እርባታ፣የኮምፖስት ዝግጅት እንዲሁም የአንኮበር የመድኃኒት እጽዋት ምርምሮች ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን በማሳየነት ጠቅሰዋል። ከኢንዱስትሪ ባለሀብቶች ጋር በመቀናጀት የኢንዱስትሪ ዩኒቨርሲቲ ትስስርን ለማጠናከር ጅምር ሥራዎች እንዳሉም አንስተዋል። እንደ አገር ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ዩኒቨርሲቲው ብቁ እና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል በማፍራት የድርሻውን እየተወጣ ነው መሆኑን ነው ምክትል ፕሬዝዳንቱ የተናገሩት። በዚሁ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሳምንት ቀን የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ተማሪዎች እንዲሁም አምራች ኢንዱስትሪዎችና ተመራማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።  
በኢትዮጵያ የኪነጥበብ ኢንዱስትሪው ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያለውን ሚና ለማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር ይገባል-የኪነጥበብ ባለሙያዎች
Jun 1, 2023 52
አዲስ አበባ ግንቦት 24/ 2015 (ኢዜአ) በኢትዮጵያ የኪነ ጥበብ ኢንዱስትሪው ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያለውን ሚና ለማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የኪነ-ጥበብና ስነ-ጥበብ ፈጠራን ለማሳደግ የሚያስችል የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በውይይቱ በኪነጥበብና ስነ ጥበብ የስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ የመወያያ የመነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የማኑፋከቸሪንግ ልማት ባለሙያ አቶ በኃይሉ ዓለማየሁ፤ የጥበብ ኢንዱስትሪ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገትና ለዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ረገድ እምቅ አቅም ያለው ዘርፍ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ፈርጀ ብዙ የባህል ኪነጥበብ ቢኖራትም በሚፈለገው ልክ ባለማደጉ ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያለው አበርክቶ አነስተኛ ሆኖ መቆየቱን ጠቅሰዋል። ሆኖም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዘርፉ እየተነቃቃ መምጣቱን በማንሳት በዚህም በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ያለው ድርሻ እየጨመረ መምጣቱን ነው የገለጹት። አቶ በኃይሉ የናይጄሪያ የፊልምና የሙዚቃ ኢንዱስትሪ በስራ እድል ፈጠራ ያለውን ትልቅ ሚና በተሞክሮነት ጠቅሰው፤ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት ከነዳጅ ቀጥሎ ትልቁ የገቢ ምንጭ መሆኑን አስረድተዋል። ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ በመማር የኢትዮጵያን የኪነጥበብ ኢንዱስትሪ በማጎልበት ለሀገር ልማትና ለዜጎች ተጠቃሚነት ጉልህ አስተዋፅኦ እንዲያበረክት በቅንጅት መስራት ተገቢ መሆኑን አንስተዋል። የጥበብ ስራዎች ቅጅና ተዛማጅ መብቶች ዙሪያ የመወያያ ሀሳብ ያቀረቡት የሰዋሰው መልቲ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ከፍተኛ ባለሙያ ታደሰ ኃይሉ በበኩላቸው፤ ሀገሪቱ ያላትን ዘርፈ ብዙ ባህልና እውቀቶች ለማሳደግና ተጠቃሚ ለመሆን የቅጅና ተዛማጅ መብቶች መከበር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይ ፈጠራን ለማሳደግና የሀገርን የቅጂ መብት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣንን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ነው ያመለከቱት። የሙዚቃ ባለሙያው ዳዊት ይፍሩ በበኩሉ፤ በነባርና አዳዲስ የኪነጥበብ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራቸው የቅጂ መብት ስጋቶች እንዳሉ በመጠቆም፤ አዳዲስና የተሻሉ የኪነጥበብ ፈጠራ ስራዎችን ለማውጣት የቅጂና ተዛማጅ መብቶችን ማረጋገጥ ላይ ላይ በትኩረት እንዲሰራ ጠይቋል። በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የዕደ ጥበብ ልማትና ገበያ ትስስር ማስፋፊያ ስራ አስፈጻሚ አቶ ነጋሽ በድሩ፤ መንግስት የኪነጥበብ ዘርፉን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሚና ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል። የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አወቀ ዘመነ፤ በኢኮኖሚ ያደጉ ሀገራት ለአዕምሮዊ ሃብት ጥበቃ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጡ ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያም ያልተነካውን የባህልና የጥበብ ዘርፍ ለማሳደግ በቁርጠኝነት መስራት ከሁሉም የሚጠበቅ ኃላፊነት መሆኑን ገልጸዋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በክረምቱ ከ50 ሺህ በላይ ወጣቶችን ያሳተፈ የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች ይከናወናሉ- ቢሮው
Jun 1, 2023 55
አሶሳ ግንቦት 24 / 2015(ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመጪው ክረምት ከ50 ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች እንደሚከናወኑ የክልሉ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ፡፡ በክልሉ የሻንጉል በጎ አድራጎት ማህበር በበኩሉ፤ ባለፉት ወራት ያከወናቸውን በጎ ተግባራት በመጪው ክረምትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡ የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ ሃጂራ ኢብራሂም ለኢዜአ እንዳሉት፤ ከመጪው ሐምሌ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ወራት የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች ለማከናወን አቅደዋል። በእቅዳቸው መሰረት በግል እና በማህበር የተደራጁ ከ50 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ተሳታፊ እንደሚሆኑ አስታውቀዋል፡፡ በበጎ ፈቃድ ስራ ክልሉን ብሎም የሃገሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት የሚከናወኑ ስራዎች መለየታቸውን ጠቁመዋል፡፡ ከመካከላቸውም ባለፉት ዓመታት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር በክልሉ አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚካሄድ ችግኝ ተከላና እንክብካቤ ዋነኛው እንደሆነ ወይዘሮ ሃጂራ ጠቅሰዋል፡፡ እንዲሁም አቅመ ደካሞችን የመርዳት ፣ የክረምት ትምህርት ማጠናከሪያ፣ የአካባቢ ጽዳትና ህገወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከል ከሚከናወኑት ተግባራት መካከል እንደሚገኙበት አመላክተዋል፡፡ በበጎ ፈቃድ ስራው የሚሳተፉ ወጣቶች በተጨማሪ በሚያከናውኗቸው ስራዎች ህብረተሰቡን ከመደገፍ ባሻገር የህይወት ተሞክሮዎች እንደሚቀስሙበት ጠቁመዋል፡፡ ባለፈው የበጋ ወቅት በተለይም ወጣቶች ከጸጥታ አስከባሪዎች ጎን በመቆም ለክልሉ ሠላም መመለስ ያደረጉት አስተዋጽኦ የሚበረታቱ መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ ሆኖም የወጣቶች ማህበራትን ከመደገፍ ጀምሮ የተደረው ጥረት አነስተኛ መሆኑን አመልክተው፤ ይህም በበጋው የበጎ ፈቃድ ስራ የቢሮው ዋነኛ ውስንነት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ውስንነቶችን ለማስተካከል በክረምቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ወይዘሮ ሃጂራ ገልጸዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሚገኙ የበጎ አድራት ወጣቶች ማህበራት መካከል 14 አባላትን የቀፈው የሻንጉል በጎ አድራጎት ማህበር አንዱ ነው፡፡   ማህበሩ ለትርፍ ያልተቋቋመና ዓላማው የተጎዱ ወገኖችን በመርዳት የሃገር ገጽታ መገንባት መሆኑን የማህበሩ ስራ አስኪያጅ ወጣት ፌኔት አያና ተናግራለች፡፡ በክልሉ በርካታ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ወገኖች አሉ ያለችው ወጣቷ፤ ከህብረተሰቡ የድጋፍ ገንዘብ በማሰባሰብ ለችግረኛ ወገኖች አነስተኛ መኖሪያ ቤት አሰርተው በመስጠት ባለፉት ወራት ካከናወኗቸው ተግባራት መካከል መሆኑን አስረድታለች፡፡ በመጪው ክረምትም ይኸው የበጎ ተግባር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል ወጣቷ ገልጻለች፡፡ የማህበሩ አባል ወጣት ወይንእሸት ደሳለኝ በሰጠችው አስተያየት፤ ለበጎ ፈቃድ ስራው የምናውለውን ገንዘብና ሌሎች የቁሳቁስ ድጋፎችን ከህብረተሰቡ ለማሰባሰብ ማህበራዊ ሚዲያን እየተጠቀምንበት ነው ብላለች፡፡ በበጎ ፈቃደኝነት የሚከናወኑ ተግባራት በምንም የማይተመን የህሊና እርካታ የሚሰጥ እንደሆነም ወጣቷ ለኢዜአ ገልጻለች፡፡ በሻንጉል በጎ አድራጎት ማህበር ወጣቶች የበጎ ፈቃድ የወደቀ ቤታቸው ተጠግኖ ለአገልግሎት መብቃቱን የተናገሩት ደግሞ አቶ ብርሃኑ ኪሮስ የተባሉ የአሶሳ ከተማ ነዋሪ ናቸው። በተደረገላቸው ድጋፍ ደስተኛ እንደሆኑና ለዚህም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፈው ዓመት 215 ሺህ 432 ሰዎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ከአራት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የበጎ ፈቃድ ስራዎች መከናወናቸውን ከቢሮው የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡  
በሐረሪ ክልል የስራ እድል ለመፍጠርና የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት አመራሩ ቅንጅቱን አጠናክሮ መስራት እንዳለበት ተጠቆመ
Jun 1, 2023 49
ሐረር፣ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ) በሐረሪ ክልል የስራ እድል ለመፍጠርና የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት አመራሩ ቅንጅቱን አጠናክሮ ሊሰራ እንደሚገባ የብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልጀባር መሀመድ አስገነዘቡ። በክልሉ በምግብና ሸቀጦች ላይ የሚታየውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋትና ለዜጎች የስራ እድል መፍጠር ለማስቻል ያለመ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልጀባር መሀመድ እንደተናገሩት፤ በክልሉ የሸቀጥ ዋጋን ለማረጋጋት የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ፓርቲው በክልሉ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የተካተቱበት ግብረ ሃይል በማቋቋም የግብርና ምርቶችን ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በማምጣት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲዳረስ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በክልሉ ዋጋን ለማረጋጋት እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች አበረታች ቢሆኑም ቀጣይነት ያለው ስራ ማከናወን ተገቢ መሆኑን አስምረውበታል። በተለይ የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት በሚከናወኑ ስራዎች ላይ ማነቆ የሆኑ ተግዳሮቶችን ከመቅረፍ አንጻር አሁንም ክፍተት እንደሚታይ ጠቁመው፤ ችግሮቹን ለመቅረፍ አመራሩ ተቀናጅቶ መስራት አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል። አቶ አብዱልጀባር አክለውም፤ በክልሉ በቀጣይ አምስት ወራት በሚከናወነው ንቅናቄ አመራሩ ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጎልበት ወጣቱን የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል ብለዋል። በክልሉ ለስራ እድል ማነቆ የሆኑ አሰራሮችን በባለቤትነት በመቅረፍና የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። በክልሉ በሚገኙ ገጠር ወረዳዎች ላይ ወጣቱን በግብርና ዘርፍ በማሰማራት አምራችነት እንዲጎለብት የማድረግ ስራ መጠናከር እንዳለበትም ጠቁመዋል። የክልሉ ንግድ ልማት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ቡሽራ አልይ በበኩላቸው በክልሉ አነስተኛና ቋሚ ገቢ ያላቸው ዜጎች ላይ የሚታየውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ዘንድሮ በቅዳሜ ገበያ 30 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው የግብርና ምርት ግብይት እንዲከናወን ተደርጓል ብለዋል። በተጨማሪም 696 ሺህ ሊትር ዘይት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲከፋፈል መደረጉን ተናግረዋል። ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 1 ሺህ 452 ህገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል። በቀጣይ አምስት ወራትም በክልሉ ነጻ የምርት ዝውውርን በማጎልበት፣ በቂ የምርትና የሸቀጥ አቅርቦትን በማሳደግ፣ ህገ ወጥ ነጋዴዎችንና ደላላዎችን በመከላከል ዋጋ የማረጋጋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል። የክልሉ የኢንተርፕራይዞች ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አሪፍ መሀመድ በቀጣይ አምስት ወራት ከሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር በተቀናጀ ለዜጎች የስራ እድል የመፍጠር ስራ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። በቀጣይ አምስት ወራት በግብርናና አረንጓዴ አሻራ ልማት 2 ሺህ 600 ወጣቶችን ስራ ለማስያዝ መታቀዱን ተናግረዋል።
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ከ109 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ተዘጋጅተዋል - የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ
Jun 1, 2023 44
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን ለአምስተኛው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ109 ሚሊየን በላይ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ። የመምሪያው ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ለኢዜአ እንዳሉት ለግብርና ምርታማነት በተሰጠው ትኩረት በበጋ መስኖ ስንዴና በመደበኛ የመኸር ሰብል ልማት ውጤታማ የምርት አሰባሰብ ስራ እየተከናወነ ይገኛል። በመደበኛ መስኖ ልማት ስራም ከ52 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በማከናወን 13 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ሰብል ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ14 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል። በመደበኛ የመስኖ ልማት የተቀመጠውን ግብ ከዕቅድ በላይ በማሳካት እንደ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮት፣ ሽንኩርት ሌሎች የአትክልትና ፍራፍሬ ዓይነቶችን ማልማት መቻሉንና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዞኑ የምርታማነት ልማት ስራ እየተሻሻለ መምጣቱን አመልክተዋል። በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ወራትም ከ2 ሺህ ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት የበጋ መስኖ ስንዴን በማልማት እስካሁን ከ80 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ እንደተቻለ ጠቁመዋል። ለአምስተኛው የአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ-ግብር ቅድመ ዝግጅትም እንደዞን ከ109 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኝ መዘጋጀታቸውንና ከዚህም ውስጥ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ የፍራፍሬ ችግኞች እንደሚገኝበት ነው አቶ አበራ ያስረዱት። የፍራፍሬ እጽዋቶችን ማልማት የአርሶ አደሩን የምግብ ፍጆታ በማረጋገጥ የገበያ አማራጭ መፍጠር እንደሚያስችል አመልክተዋል። ለመርሐ-ግብሩ ከ18 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኝ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በአገር አቀፍ ደረጃ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተያዘው አምስተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞች መዘጋጀታቸውን በመጠቆም፤ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞችን በብዛት እንደሚተከሉ ማሳወቃቸው የሚታወስ ነው።
የሚታይ
በሀዋሳና ጅማ አዲስ የደረቅ ወደብ ተርሚናል ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል - የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ
Jun 1, 2023 58
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፦በሀዋሳና በጅማ አዲስ የደረቅ ወደብ ተርሚናል ግንባታ ሂደቶች በቅርቡ የሚጀመሩ መሆኑን የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ድርጅት ገለጸ። የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የወደብና ተርሚናል ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ምሕረተአብ ተክሉ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ተቋሙ በአገሪቱ ለገቢና ወጪ ጭነቶች የሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ነው። የወጪና ገቢ ንግድ ፍሰት የሚመጥንና ሊያስተናግድ የሚችል የሎጂስቲክስ አቅርቦትና የደረቅ ወደብ ተርሚናል ማስፋፊያ እንዲሁም አዳዲስ የደረቅ ወደብ ግንባታ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይም ተጨማሪ የደረቅ ወደብ ግንባታ በየጊዜው እየጨመረ ሲሄድ የወጪ ገቢ ንግድ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ባለሃብቶችን ለማበረታታትና ተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅም ለመፍጠር የላቀ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል። በመሆኑም ተቋሙ በሀዋሳና በጅማ ሁለት አዳዲስ የደረቅ ወደብ ተርሚናሎች ግንባታን በጥቂት ወራት ውስጥ እንደሚጀምር ጠቅሰው፤ ለፕሮጀክቶቹ ቅድመ ግንባታ ለእያንዳንዳቸው 150 ሚሊዮን ብር በጀት ተይዞላቸዋል ነው ያሉት። ይህም በጀት ለወሰን ማስከበር፣ ማማዎችን ለመገንባት፣ ጊዜያዊ ቢሮዎችን ለማቋቋምና ሌሎች ተያያዥ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ሥራዎችን ለማከናወን እንደሚውል ጠቁመዋል። የቀጣይ ምዕራፍ ግንባታም የቢዝነስ ጥናቱን ተከትሎ ተጨማሪ በጀት በመመደብ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በተለይም የሀዋሳ ደረቅ ወደብ ግንባታ ከአምስት ዓመታት በፊት የተጀመረ መሆኑን አንስተው፤ ከመሬት አቅርቦት ጋር ተያይዞ ለረዥም ጊዜ መጓተቱን አስረድተዋል። ይህም ሆኖ አሁን ላይ እነዚህ ችግሮች እልባት አግኝተው የግንባታ ሥራ ለመጀመር የቢዝነስ ጥናቱ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በ3 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፈው ይኸው የሀዋሳ የደረቅ ወደብ በቀጣዩ በጀት ዓመት መጀመሪያ የግንባታ ሥራው ይጀመራል ብለዋል። በሃያ ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፈውን የጅማ ደረቅ ወደብ ተርሚናል ግንባታ ለመጀመር የመሬት አቅርቦት በአጭር ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁን ገልጸዋል። የግንባታ ዲዛይኑ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ዓመት መጀመሪያ ግንባታው እንደሚጀመር ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በስምንት የደረቅ ወደቦች ላይ በደንበኞች ፍላጎትና የሎጂስቲክስ አገልግሎቱን ለማሳለጥ በሚያስችል መልኩ የማስፋፊያ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ተቋሙ የሚያከናውናቸው የአዳዲስ ደረቅ ወደብ ግንባታዎችና የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች የአገሪቱን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማሳለጥ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ነው ያስረዱት።
በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ ውጤታማ የልማት ሥራዎችን በማስቀጠል የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሁሉም ጥረት ሊታከልበት ይገባል- ዶክተር ፍጹም አሰፋ
Jun 1, 2023 107
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ) በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ ውጤታማ የልማት ሥራዎችን በማስቀጠል የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሁሉም ጥረት ሊታከልበት ይገባል ሲሉ የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽን ሚያዝያ 29 ቀን 2015 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተመርቆ ለጎብኝዎች ክፍት መሆኑ ይታወቃል። በዚህም እስካሁን የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ሌሎችም ኤግዚቢሽኑን ጎብኝተዋል። በዛሬው እለትም የፌደራልና የክልል የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አውደ-ርዕዩን ጎብኝተዋል።   ከጉብኝቱ ተሳታፊዎች መካከል የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ዶክተር ፍጹም አሰፋ፣ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና ሌሎችም የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ከጉብኝቱ ጎን ለጎንም በሲዳማ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች የተዘጋጀውና በሌማት ትሩፋት የተገኙ ውጤቶችን የሚያስቃኝ አውደ-ርዕይን በሳይንስ ሙዚየም መርቀው ከፍተዋል። በሁለቱ ክልሎች የተዘጋጀው አውደ-ርዕይ ላይ የዓሳ፣ የማር፤ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የቅመማቅመም፣ የእንስሳት ተዋጽዖዎችን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ውጤቶች ለዕይታ ቀርበዋል። በኢትዮጵያ በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴና የአረንጓዴ ልማት መርሃ-ግብሮች ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገልጸዋል። በኩታገጠም የአስተራረስ ዘዴ እያደገ የመጣው የግብርና ሜካናይዜሽን ጋር ተዳምሮ ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ መሆኗን በተግባር እያየን ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ለዘመናት ከውጭ ይገባ የነበረውን ምርት በማስቀረት ለውጭ ገበያ ጭምር ማቅረቧ የውጤታማነቱ ሁነኛ ማሳያ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ ውጤታማ የልማት ሥራዎችን በማስቀጠል የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሁሉም ጥረት ሊታከልበት ይገባል ብለዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፤ የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ የግብርናው ዘርፍ በእውቀትና በቴክኖሎጂ ከተመራ ስኬታማ መሆን እንደሚቻል ጥሩ ማሳያ ነው ብለዋል።   በክልሉ በተለይም በቡና፣ ሰሊጥ፣ ቅመማቅመም፣ ማርና የእንስሳት ተዋጽኦ ሰፊ ኃብት መኖሩን ጠቅሰው፤ በአግባቡ ማልማት ከተቻለ አገር መለወጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። በሁሉም አካባቢዎች ኢትዮጵያ ኃብቷን ማልማት ከቻለች እድገትና ብልጽግናዋን በአጭር ጊዜ ማሳካት ያስችላልም ነው ያሉት። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በግብርናው መስክ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ለአገር እድገትና ለዜጎች የኑሮ መሻሻል ትልቅ ተስፋ የሰነቀ መሆኑን ገልጸዋል።   በሲዳማ ከክልል ባለፈ ለአገራዊ ኢኮኖሚ እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከት የሚያስችል እምቅ ኃብት በመኖሩ የልማት ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው፤ የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይን እስካሁን ከ50 ሺህ በላይ ሰዎች የጎበኙት መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣዩ እሑድ የሚጠናቀቅ መሆኑን ጠቁመዋል። አውደ-ርዕዩ የግብርናውን ዘርፍ የሚያጠናክር ትልቅ ውጤት የተገኘበት መሆኑን ገልጸው፤ የጎብኝዎችም ፍላጎትና ተነሳሽነት ከተገመተው በላይ መሆኑን ተናግረዋል።   በግብርና ሚኒስቴር፣ በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት እና ኢትዮ-ቴሌኮም በጋራ የተዘጋጀው የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ የግብርናው ዘርፍ ያለበትን ደረጃ የሚያሳዩ ምርቶች፣ የግብርና ቴክኖሎጂዎች እና የምርምር ውጤቶች ቀርበውበታል።  
አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት እንዲፈረም ጠየቁ
Jun 1, 2023 77
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ጠየቁ ሚኒስትር ዴኤታው ዛሬ በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። አምባሳደር ምስጋኑ በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈረም የሚደረገው ዝግጅት እንዲፋጠን ጠይቀዋል። የሁለቱ አገራት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በሚጀመርበት ሁኔታ ዙሪያም ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከወዲሁም አስፈላጊ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት እና ለማቋቋም እየተደረገ ያለውን ጥረት የኩዌት መንግስት እንዲደግፍም አምባሳደር ምስጋኑ ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢ በበኩላቸው በሁለቱ ሃገራት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የኩዌት መንግስት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የኩዌት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባው እንዲጀመር አስፈላጊውን ጥረት እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።
አገራት በሳይበር ምህዳሩ ዘላቂ የሆነ ጥቅም ለማግኘት ትውልድ ተሻጋሪ የአቅም ግንባታ ስራ መስራት ይገባቸዋል - አቶ ሰለሞን ሶካ
Jun 1, 2023 73
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፦ አገራት በሳይበር ምህዳሩ ዘላቂ የሆነ ጥቅም ለማግኘት ትውልድ ተሻጋሪ የአቅም ግንባታ ስራ መስራት እንደሚገባቸው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። በሞሮኮ እየተካሄደ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን የያዘ ሲሆን "የሳይበር ደህንነት አቅም ግንባታ ስራ ለሙያዊ ልህቀትና ለኢኮኖሚ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት ተደርጓል። በአውደ ርዕዩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በትውልድ መካከል የሚፈጠሩ የእውቀት ክፍተቶችን ለመሙላት ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል። እንደ ኢመደአ ያሉ የሳይበር ምህዳር ላይ የተሰማሩ ተቋማት የሰው ኃይል አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ድጋፍ መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢመደአ ብቁ እና ወሳኔ ሰጪ አመራር ለማፍራት የሚያስችሉ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል። የሰው ኃይልን ከትምህርት የተመረቁ ብቻ ይዞ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና ቀጣይነት ያለውን የበቃ የሰው ሃይል ልማት ማስቀጠል ስለማይቻል ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች መልምሎ እና እውቀታቸውን ለማጎልበት መስራት እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት። በተያያዘም የሳይበር ጥቃት ከዓለማችን ቀዳሚ ስጋቶች አንዱ መሆኑንና ምህዳሩ ፍጹም ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች እንደሆነ ተናግረዋል። ከዚህ አንጻር አገራት በሳይበር ምህዳሩ ላይ በሚሰሩ ስራዎች ላይ በትብብርና በቅንጅት ሊሰሩበት እንደሚገባ መግለጻቸውን ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ ነገ ይጠናቀቃል።          
የታክስና የጉምሩክ ሕግ ተገዥነትን በማረጋገጥ ለአገር ዘላቂ ልማትና የሕዝብ ተጠቃሚነት ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል - የገቢዎች ሚኒስቴር
Jun 1, 2023 60
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ)፦ የታክስና የጉምሩክ ሕግ ተገዥነትን በማረጋገጥ ለአገር ዘላቂ ልማትና የሕዝብ ተጠቃሚነት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ የገቢዎች ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ። የገቢዎች ሚኒስቴር ከየካቲት እስከ የካቲት "ግብር ለአገር ክብር" በሚል መሪ ሃሳብ በታክስ እና የጉምሩክ ሕግ ተገዥነት ላይ ያተኮረ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ንቅናቄ በማካሄድ ላይ ይገኛል። የሚኒስቴሩ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አዲሱ ይርጋ በታክስ ዙሪያ የኅብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ በአገር አቀፍ ደረጃ የንቅናቄ መርሃ-ግብር እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ለዘርፉ ስኬት በተለይም የኅብረተሰቡ እገዛና ጠንካራ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለሀገር ልማትና ለሕዝብ ተጠቃሚነት በጋራ ልንሰራ ይገባል ብለዋል። በመሆኑም የታክስ ስወራና ማጭበርበርን በመከላከል የኢትዮጵያን ዘላቂ ልማት መደገፍ የሁሉም ዜጋ አገራዊ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ነው ያሉት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ። የንቅናቄ መርሃ-ግብሩ የኅብረተሰቡን ተሳትፎ በማሳደግ ረገድ የራሱን አስተዋጽዖ እያበረከተ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። በመሆኑም የኅብረተሰቡና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ይበልጥ በማጠናከር በዘርፉ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ይሰራል ብለዋል። ከታክስ ጋር በተያያዘ አብዛኛው የሕግ ጥሰት የሚፈጸመው ሕግን ባለማወቅና ከግንዛቤ እጥረት መሆኑን ጠቅሰው በወንጀሉ የሚሳተፉ አካላትን በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ ቅንጅታዊ ሥራዎች በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላሉ ነው ያሉት። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግንቦት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረትና በታክስ ላይ የሚፈጸመውን ማጭበርበር ለመከላከል የቀረበውን አዋጅ ማጽደቁ ይታወቃል።  
ማስታወቂያ
ፖለቲካ
አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት እንዲፈረም ጠየቁ
Jun 1, 2023 77
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ጠየቁ ሚኒስትር ዴኤታው ዛሬ በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። አምባሳደር ምስጋኑ በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈረም የሚደረገው ዝግጅት እንዲፋጠን ጠይቀዋል። የሁለቱ አገራት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በሚጀመርበት ሁኔታ ዙሪያም ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከወዲሁም አስፈላጊ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት እና ለማቋቋም እየተደረገ ያለውን ጥረት የኩዌት መንግስት እንዲደግፍም አምባሳደር ምስጋኑ ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢ በበኩላቸው በሁለቱ ሃገራት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የኩዌት መንግስት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የኩዌት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባው እንዲጀመር አስፈላጊውን ጥረት እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።
ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 
Jun 1, 2023 97
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚጠበቅባቸውን ሚና በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ጋር በመተባበር ለአገር ውስጥና ለውጭ ጋዜጠኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና እየሰጠ ነው። ሥልጠናው መገናኛ ብዙኃን ጸጥታና ደኅንነት በማረጋገጥ እንዲሁም ድንበር ዘለል የጸጥታ ሥጋት በመከላከል ሚናቸውን ማጎልበት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ትኩረት አድርጓል ተብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው እንቅስቃሴ ዲፕሎማቶች ብቻ ሳይሆን ጋዜጠኞችም ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። በመሆኑም ጋዜጠኞች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ገልጸው በተለይም ደግሞ ትክክለኛ መረጃዎችን በማሰናዳት ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት።   የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ጀማላዲን መሃመድ በበኩላቸው ሥልጠናው ጋዜጠኞች በጸጥታ ጉዳዮች ያላቸውን ግንዛቤ ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል። በተለይም በግጭትና በፀጥታ ጉዳዮች ላይ ኃላፊነት በተሞላበት አኳኋን እንዲሰሩ እንዲሁም ትክክለኛና ሚዛናዊ ዘገባዎችን ለማቅረብ አስፈላጊውን እውቀትና ክህሎት ለማዳበር የሚረዳ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የኢጋድ አባል አገራት ድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ ሥጋቶችን ለመቅረፍ የአባላትን አቅም ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ጋዜጠኞች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እንደሚረዳ ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) የጸጥታና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ፤ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና በበርካታ ድንበር ዘለል የጸጥታና ደኅንነት ሥጋቶች ያሉበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም መገናኛ ብዙኃን በቀጠናው የሚያጋጥሙ የጸጥታ፣ ደኅንነትና ወንጀል ሥጋት በአግባቡና በትክክለኛው መንገድ በመገንዘብ ገጽታ የሚገነቡና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስከብሩ ሥራዎችን በትኩረት መሥራት አለባቸው ነው ያሉት። በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ደኅንት ማረጋገጥ ብዙኃኑን ያሳተፈ ሁለገብ ሥራን የሚጠይቅ በመሆኑ በዚህ ረገድ የመገናኛ ብዙኃን የድርሻቸውን ጉልህ ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተጠቁሟል። የመገናኛ ብዙኃን ግጭትን መከላከል ብቻ ሳይሆን በድህረ ግጭት የሰላም ግንባታ እንዲሁም ደግሞ ሰላም በዘላቂነት እንዲረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ነው ያሳሰቡት።            
አገራዊ ምክክሩ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት መደላድል የሚፈጥር ነው - የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች  
May 31, 2023 90
ድሬዳዋ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ):- አገራዊ የምክክር መድረኩ ብሔራዊ መግባባት በመፍጠርና አንድነትን በማጠናከር የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት መደላድል እንደሚፈጥር የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች ገለጹ። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአገራዊ የምክክር ሂደት ላይ አጀንዳ ለማሰባሰብ ስለሚከናወኑ ተግባራትና የውይይት ተሳታፊዎች ልየታን አስመልክቶ በድሬዳዋ ለሁለት ቀናት ያዘጋጀው ስልጠና ተጠናቋል ። በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች እንዳሉት በአገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው የምክክር መድረክ ብሔራዊ መግባባት የሚፈጥር ወሳኝ የሽግግር ምዕራፍ ነው። ከድሬዳዋ መምህራን ማህበር የመጡት መምህርት ሙሉካ ሁሴን ስልጠናው በቀጣይ በሚካሄደው አገራዊ ምክክር ተሳታፊዎችን የመለየት ሂደት ተአማኒነትና አሳታፊነትን ያሟላ ለማድረግ እንደሚያስችል ገልጸዋል። “በአገር ደረጃ የሚካሄደው የምክክር መድረክ በዜጎች መካከል መቀራረብ እና አንድነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ከፍታ ለማረጋገጥ ያስችላል” ብለዋል። አገራዊ የምክክር መድረክ አገራዊ መግባባት ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የድሬዳዋ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዮናስ በትሩ ናቸው። በሰከነ መንፈስ መወያየት ለአገር ዘላቂ ሰላምና እድገት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንና የጋራ ምክር ቤቱ በቀጣይ የሚካሄዱ የምክክር ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ ይሰራል ብለዋል። የድሬዳዋ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ጥምረት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አንድነት ዘነበ "ኢትዮያዊያን የሚያካሂዱት ምክክር አገራዊ አንድነትን ለማጠናከር መሰረት የሚጥል ነው" ብለዋል። የምክክር መድረኩ ኢትዮጵያዊያን በራሳቸው አጀንዳዎች ላይ መግባባት የሚፈጥሩበት ብቻ ሳይሆን አንድነትና አቅም መፍጠር የሚያስችላቸው መሆኑን አመልክተዋል።   የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር እንዳሉት ኮሚሽኑ በሚያከናውነው የተሳታፊዎች ልየታ የተለያዩ ተቋማት እና ባለድርሻ አካላት የሂደቱን ግልጸኝነት ፣አሳታፊነትና ተአማኒነት የመታዘብና የማረጋገጥ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። የምክክር መድረኩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጨምሮ ሁሉንም የሚያሳትፍ በመሆኑ ብሔራዊ መግባባት በመፍጠር ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። በሰከነ መንገድ በመወያየት የጋራ አገራዊ መግባባት በመፍጠር ኢትዮጵያን ለማሻገር እንደሚያስችል አመልክተዋል።  
ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየሰሩ እንደሚገኙ የአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሚኖሩ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ገለጹ
May 31, 2023 84
ደብረ ብርሃን ግንቦት 23 / 2015 (ኢዜአ):- አብሮነትን በማጠናከር የአካባቢያቸውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ እየሰሩ እንደሚገኙ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሚኖሩ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች አስታወቁ። በአማራ ክልል የአንጎላላ ጠራ ወረዳ እና በኦሮሚያ ክልል የቅንቢቢት ወረዳ ነዋሪዎች በአካባቢያቸው ዘላቂ ሰላምን ማስፈንና ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የጋራ ውይይት ዛሬ አካሄደዋል። ከአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አጎላላ ጠራ ወረዳ ተሳታፊ የሆኑት መላከ መዊዕ ቀሲስ ገዛኸኝ ኃይሉ እንደገለጹት፤ የአማራና የኦሮሞ ሕዝብ በአንድነት፣ በፍቅር እና በመተሳሰብ የሚኖር ነው። ለሕዝቡ ሰላምን፣ ፍቅርን፣ አንድነትንና መተሳሰብን መሰረት አድርገው በማስተማር የአካባቢያቸው ሰላም በዘላቂነት እንዲጠበቅ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ከኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቅንቢቢት ወረዳ የመጡት ቄስ ተሰማ በላቸው በበኩላቸው በሕዝቦች መካከል ፍቅርና ሰላም ጸንቶ እንዲዘልቅ ወጣቶችን እያስተማርን ነው ብለዋል። የሕዝቦች አብሮ የመኖር እሴት እንዲጎለብትና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በማስተማር የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።   ከቅንቢቢት ወረዳ የመጡት የአገር ሽማግሌ አቶ ተስፋዬ ግርማ በበኩላቸው በአካባቢው የሚኖሩ የኦሮሞ እና የአማራ ህዝቦች ከትውልድ ትውልድ የተሻገረ የጋራ ታሪክና እሴት እንዳላቸው አውስተዋል። "የብሔር ልዩነት ሳይገድበን አብረን የምንኖር ሕዝቦች በመሆናችን የጀመርነውን የጋራ እድገት፣ ልማትና ዘላቂ ሰላም የማረጋገጥ ጥረት አጠናከክረን እንቀጥላለን" ብለዋል። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት የአገር ሽማግሌ አቶ ተስፋዬ ሞገስ በበኩላቸው ከኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ ወረዳ ሕዝቦች ጋር በፍቅርና በሰላም የምንኖረው በመማከርና በመወያየት ነው ሲሉ ገልጸዋል። አለመግባባቶች ሲኖሩ የአገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ጋር በመመካከር እየፈቱ እንደሚገኝና በዚህም የአካባቢው ሰላም ተጠብቆ መቆየቱን ተናግረዋል። "የአካባቢያችንን ሰላም ለማደፍረስ የሚጥሩ ኃይሎችን እኩይ ሴራ ቀድሞ በማክሸፍ ሰላሙ ጽንቶ እንዲዘልቅ በጋራ የጀመርነው ውይይትና ምክክር ተጠናክሮ ይቀጥላል" ብለዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች ከአካባቢያቸው ባለፈ በአገር አቀፍ ደረጃ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ መንግስት የሚያደርገውን ጥረት በመደገፍ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።    
የሲዳማ ክልል የህዝብ አደረጃጀቶች የህዝብ ጥያቄዎች ለአገራዊ ምክክር መድረክ እንዲቀርቡ ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡ ገለጹ 
May 31, 2023 81
ሀዋሳ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ) የህዝብ ጥያቄዎች ለአገራዊ ምክክር መድረክ እንዲቀርቡ ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡ በአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በተባባሪነት የተለዩ የሲዳማ ክልል የህዝብ አደረጃጀቶች አስታወቁ። ኮሚሽኑ በተሳታፊ ልየታና አጀንዳ መረጣ ላይ ለሚሳተፉ ተባባሪ አካላት በሀዋሳ ከተማ ባዘጋጀው ስልጠና ላይ የተሳተፉ የሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የእድርና ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የኮሚሽኑ ስራ በስኬት እንዲጠናቀቅ የዜጎች ያልተቆጠበ ተሳትፎ ያስፈልጋል። በመሆኑም በምክክሩ የሚሳተፉ የህብረተሰብ ተወካዮችን የመምረጥ ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እንደሚወጡ ገልጸዋል። በሲዳማ ክልል ሴቶች ማህበር የሲቪክ ማህበረሰብ ተወካይ ወይዘሮ ዘውዲቱ ጥላሁን በአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለሚከናውነው ታላቅ ተልእኮ በተባባሪነት መመረጣቸው ከፍተኛ ሃላፊነት እንደሆነ ገልጸዋል። ይህን ሃላፊነት በአግባቡ በመወጣት እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ያሉ ሴቶች ድምጽ እንዲሰማ ለማድረግ የሴቶችን ተሳትፎ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በሰላም ማጣት የበለጠ ተጎጂ ከሚሆኑት ማህበረሰብ ክፍሎች ሴቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በሂደቱ ሴቶች በንቃት እንዲሳተፉ ለማስቻል እንሰራለን ብለዋል። የመልጋ ወረዳ አካል ጉዳተኞች ማህበር ሰብሳቢ አቶ ሃየሶ ሃሶ በበኩላቸው በብሄራዊ ምክክር ሂደቱ የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ እንዲኖር መደረጉ በርካታ ችግሮችን ለመቅረፍ ያስችላል ብለዋል።   በስልጠና መድረኩ ያገኙትን ግንዛቤ ተጠቅመው በምክክር መድረኩ ተገቢውን ሃሳብ ሊያንሸራሽሩ የሚችሉ ተወካዮችን በመምረጥ ከብሄራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ጋር እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመፍታት የሀገርን ህልውና ለማስቀጠል የብሄራዊ ምክክሩ አስፈላጊነት በዜጎች ቅቡልነት ያገኘ ነው ያሉት ደግሞ የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተወካይ አቶ ሃብተማርያም አብዩ ናቸው። የማያስማሙን ጉዳዮች ቢኖሩ እንኳን በአገር ሰላምና አንድነት ላይ ባለመደራደር የንግግር ባህልን ማሳደግና ከችግሩ ለመውጣት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በሀዋሳ ከተማ የመሀል ክፍለ ከተማ እድር ተወካይ አቶ መስፍን ዘውዴ በበኩላቸው አገራዊ ምክክሩ ለግጭት መንስኤ እየሆኑ ላሉ በርካታ ችግሮች መፍትሄ የሚሰጥ በመሆኑ ብርቱ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። እድሮች የተለያየ ህብረተሰብ ክፍል የሚሳተፍባቸው እንደመሆናቸው መጠን ለሀገር ጠቃሚ ሃሳቦችን ማመንጨት እንደሚችሉ አመልክተዋል። በመሆኑም የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ አካላትን በመምረጥ የህዝቡን ችግር በተገቢው የሚያሳይ አጀንዳ ለመምረጥ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ብሄራዊ ምክክር ኮሚሽን በሲዳማ ክልል በአጀንዳ ማሰባሰብና ምክክር ላይ የሚሳተፉ አባላትን ለሚመለምሉ ተባባሪ አካላት በሀዋሳ ስልጠና መስጠቱ ይታወሳል።
ብልፅግና ፓርቲ በሰጠው ጠንካራና ቅቡልነት ያለው አመራር የሀገረ መንግስት ግንባታን የሚያፋጥኑ ስራዎች ተከናውነዋል - የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ
May 31, 2023 108
አዲስ አበባ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ)፦ብልፅግና ፓርቲ በሰጠው ጠንካራና ቅቡልነት ያለው አመራር የሀገረ መንግስት ግንባታን የሚያፋጥኑ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳን አቶ አደም ፋራህ ገለጹ። ፓርቲው የተጀመሩ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ዲፕሎማሲያዊ ስራዎች በስኬት እንዲቀጥሉ የፓርቲውን አመራር የማጥራት፣ የማጠናከርና የመገንባት ስራ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ በቆየው መደበኛ ስብሰባ ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎችና ነገ የሚጀመረውን የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ በማስመልከት ለኢዜአ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በዲፕሎማሲያዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ገምግሞ የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል ብለዋል፡፡ በፖለቲካው ዘርፍ የጋራ መግባባት ያልተደረሰባቸው መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን በምክክር ኮሚሽኑ አማካኝነት በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመፍታት የተጀመረው ጥረት መልካም መሆኑ ተገምግሟል ነው ያሉት፡፡ የብልጽግና ፓርቲም ሁሉንም አሳታፊ ውይይት እንዲደረግ እና የጋራ ብሔራዊ መግባባት ላይ እንዲደረስ እንደ አንድ ፓርቲ የበኩሉን ሚና እንዲያበረክት አቅጣጫ መቀመጡን አንስተዋል፡፡ ፓርቲው በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ስርዓትን ለማንበር በርዕዮትና በፖሊሲ የሚለዩትን የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመንግስት መዋቅር ውስጥ በማሳተፍ የትብብር መንፈስ እንዲፈጠር አድርጓል፤ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ዘላቂና አወንታዊ ሰላም ለመፍጠር ለህዝብ ጥቅም የቆሙ ነፃና ገለልተኛ የጸጥታና ደህንነት እንዲሁም የዴሞክራሲ ተቋማትን በመገንባት አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ የትጥቅ ትግል ሲያካሂዱ ከነበሩ አካላት ጋር ዘመናዊና ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ያጣመረ ውይይት በማካሄድ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጥረት መደረጉ በስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በአዎንታዊነት እንደተገመገመ ጠቅሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የቡድንና የግል ፍላጎትን በኃይል ለማሳካት ያሰቡ ጽንፈኛ አካላት ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን እየፈተኑት ነው ያሉት አቶ አደም፤ ነፃነትን ለመጠቀም የሌሎችን ነፃነት ማክበር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የህግ የበላይነትንና ህገ መንግስታዊነትን ማረጋገጥ፣ የተሟላ ሀገራዊ ሰላምን ማፅናት፣ የፍትሕና ፀጥታ ተቋማትን ማጠናከር፣ የሁለም ኢትዮጵያውያን የወል እውነቶችን ገዥ ቦታ እንዲይዙ ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ ማስቀመጡን ተናግረዋል። ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ባለፉት 10 ወራት ፍትሐዊ ልማትን ከማረጋገጥ አንጻር አካታች ኢኮኖሚ እየተገነባ መሆኑን በውይይቱ እንደተመለከተም አብራርተዋል። የብዝኃ ዘርፍ የኢኮኖሚ ስርዓትን በማስቀጠል የተመዘገቡ ስኬቶች መኖራቸውን ገልጸው፤ በተለይም በስንዴ ምርታማነት የታየውን ውጤት በትልቅ ስኬት ማነሳቱን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ችግር በመፍታት፣ ምርታማነትን ለማሳደግና የገበያ ትስስር በመፍጠር አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ በገበታ ለሀገር እና ሌሎች ፕሮጀክቶች የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት መቻሉን እንዲሁም ከስራ ዕድል ፈጠራ አኳያ በዘጠኝ ወራት ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የዋጋ ንረትን ለማረጋገት፣ ኮንትሮባንድን ለመከላከል፣ በአምራችና ሸማቹ መካከል እሴት የማይጨምሩ የገበያ ሰንሰለቶችን ለመቀነስ ጠንካራ ርምጃዎች እንዲወሰዱ አቅጣጫ ማስቀመጡን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ አካታች የማህበራዊ ልማትን ለማጎልበት በትምህርት፣ በጤና እንዲሁም በወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይ አበረታች ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም በማህበራዊ መስክ ያሉ የትምህርት ጥራት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተጠቃሚነትን መሰረተ ያደረገ ሥነ ምግባራዊና ሀገር ውዳድ ትውልድ ግንባታ ይከናወናል ብለዋል፡፡ ትብብርና የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ የዲፕሎማሲ ስራዎች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰው፤ ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ በመስጠት የኢኮኖሚ ትስስር ፣ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲጠናከር የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። የሀገርን ክብር የማስጠበቅ አካሄዳችን ያልተመቻቸው አካላት የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ የፈጠሩብንን ጫና በመቋቋም የሀገር ሉዓላዊነታችንና የግዛት አንድነታችንን አስጠብቀን ቀጥለናል ብለዋል፡፡ ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ የመስጠት መርህ ውጤት በማስገኘቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ በቀጣይም ሚዛኑን የጠበቀ ሁሉን አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ አካሄድን በመከተል የፖሊሲ ነጻነታችንን የሚጋፉና ፍትሐዊ ተጠቃሚነታችንን እንዳናረጋገጥ የሚፈትኑ ጫናዎችን የመመከትና ወዳጅነትን የማስፋት ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ መቀመጡን አንስተዋል። ብልጽግና ፓርቲ የተጀመሩ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ዲፕሎማሲያዊ ስራዎች በስኬት እንዲቀጥሉ የፓርቲውን አመራር የማጥራት፣ የማጠናከርና የመገንባት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ ፈጠራና ፍጥነትን ተጠቅሞ የፓርቲውን አደረጃጀት ማጠናከር፣ የውስጠ ፓርቲ አንድነትና ዴሞክራሲን ማጎልበት፣ ብሎም በምርጫ ወቅት ለህዝብ የተገባውን ቃል በውጤታማነት መፈጸም የቀጣይ ትኩረት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ለዘላቂ ሰላም መስፈን የድርሻቸውን እንደሚወጡ የጌዴኦ ዞን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ
May 31, 2023 84
ዲላ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ) ለዘላቂ ሰላም መስፈን የድርሻቸውን እንደሚወጡ የጌዴኦ ዞን የቤተ እምነት መሪዎችና የባህል አባቶች አስታወቁ። የሰላም እሴቶችን ለማጽናትና ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልን ዓላማው ያደረገ የሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ የሚመክር መድረክ ዛሬ በዲላ ከተማ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የቤተ እምነት መሪዎች፣ የባህልና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ አስተዳደር የስራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል በኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን የልማት ካውንስል ዳይሬክተር መጋቢ ቦካኮ ዱጉማ እንዳሉት ስለ ሰላም መስራት የቤተ እምነቶች ተቀዳሚ ተልዕኮ ነው። "ልጆቻችንን ስናሳደግ ጥላቻና በደል እያስተማርን ሳይሆን ለሀገርና ለወገን የሚበጀውን ስለ ፍቅር፣ ሰላም፣ አብሮነትና አንድነትን በመመገብ ሊሆን ይገባል" ብለዋል። በተለይም ታሪክን ለአገር ግንባታና ለትውልድ ትምህርት መውሰድ እንጂ የጠብና የግጭት ምንጭ አድርገን መተረክ እንደማይገባ አስገንዝበዋል። የቋንቋና የሃይማኖት ልዩነቶች ውበትና ጸጋዎች መሆናቸውን ተረድተን ከአክራሪነትና የኔ ብቻ ከሚል ጽንፈኝነት ይልቅ ለሰላምና ለመቻቻል ቅድሚያ መስጠት ይገባል ብለዋል። በተለይም በሀገራችን የመጣውን የሰላም አየር ዘላቂና ወንድማማችነትን ያጎለበተ እንዲሆን ግንባር ቀደም ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል። የጌዴኦ ብሔር ባህላዊ የባሌ አስተዳደር መሪ አባ ገዳ ቢፎሚ ዋቆ በበኩላቸው በሀገራችን የሚገኙ በርካታ ባህሎች ለሰላም ግንባታ ጠቃሚ እሴቶች ያሉ ቢሆንም በአግባቡ ከመጠቀም አንጸር ውስንነቶች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። የባህል አባቶችና የቤተ እምነት መሪዎች "ግጭትን ለማስቀረት የምናደርገውን ጥረት ያክል ያገኝነውን የሰላም አየር ዘላቂ ለማድረግም ልንሰራና ልንጥር ይገባል" ብለዋል። በተለይም በውስጣችን ለግጭት መነሻ የሆኑ አስተሳሰቦችን በውይይት የመፍታት ባህላችንን በማሳደግ ለትውልዱም ሆነ ለሀገራችን የፖለቲካ ስርዓቱ ምሳሌ መሆን ይጠበቅብናል ሲሉም ተናግረዋል። የሰላም እሴቶችን ማስተዋወቅና ማስተማር ለዘላቂ ሰላም መሰረት መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የጌዴኦ ዞን የሃይማኖት ተቋማት ካውንስል ሰብሳቢ ቄስ አያሌው ሙርቲ ናቸው። የተለያዩ ሃይማኖት ተከታዮች ከጥላቻና መገፋፋት ይልቅ ወንድማማችነትንና ወዳጅነትን እንዲያስቀድሙ የጋራ እሴቶች ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ምስጋና ዋቀዮ በበኩላቸው በሀገራችን የመጣውን የሰላም ሁኔታ ሊያሻክሩ የሚችሉ ጽንፈኝነትን በጋራ መከላከል ይገባል ብለዋል። በተለይም በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ጥላቻና ግጭትን የሚሰብኩ የፖለቲካ ነጋዴዎች ተቀባይነት እንዳያገኙና ትውልዱን በሰላም እሴቶች በመገንባቱ ረገድ የቤተ እምነት መሪዎችና የባህል አባቶች ድርሻቸው የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአንጻሩ ወንድማማችነትን የሚያጎለብቱ መድረኮችን በማጠናከር ሀገራዊ ሰላማችንን ዘላቂ በማድረጉ ረገድ የድርሻቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተስፋጽዮን ዳካ በበኩላቸው በህብረተሰቡ ዘንድ መግባባት እና መተማመን በመፍጠር ፍፁም የሆነ ሰላም ማምጣት እንደሚቻል አመላክተዋል። ከግጭት የሚያተርፉ አካላት መቼውንም ጊዜ ለሰላም ፍላጎት የሌላቸው በመሆኑ የጋራ ትግል ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል። መሰል የሰላም ግንባታ ስራዎች ደግሞ ወጣቱን በይበልጥ ተሳታፊ ማድረግ እንዳለበት ጠቅሰው፤ በተለይ አባቶች ትክክለኛውን ታሪክ ለትውልድ በማስተላለፍ ለሰላም ግንባታ በሚደረገው ጥረት አጋዥ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።    
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለእጀባ ለበረራ ደህንነትና ቁልፍ የመሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ የሰው ኃይሉን በተከታታይ ስልጠናዎች እያበቃ መሆኑ ተገለጸ
May 31, 2023 82
አዲስ አበባ ግንቦት 23/2015(ኢዜአ)፦የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የሀገር መሪዎችን፣ ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ከአደጋ የመጠበቅና የበረራ ደኅንነትን የማረጋገጥ ተልዕኮውን በብቃት ለመፈጸም የሰው ኃይሉን በተከታታይ ስልጠናዎች እያበቃ መሆኑን ገለጸ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለሪፐብሊካን ጋርድና ለአገልግሎት መስሪያ ቤቱ እጀባ ፣ለበረራ ደኅንነት መኮንኖችና አመራሮች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን አስመርቋል። አገልግሎቱ ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መረጃ እንዳመለከተው በትብብርና በአጋርነት አብረውት ከሚሰሩ የውጭ መረጃና ደኅንነት ተቋማት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ይህ ስልጠና በዋናነት በቪአይፒ ደኅንነት ጥበቃ፣ በፈንጂ ምህንድስና ፣በድሮን አጠቃቀም ቅየሳና የአደጋ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ያተኮረ ነው። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ በምረቃው ላይ እንደገለጹት አደጋ መቼና እንዴት እንደሚከሰት በእርግጠኝነት መናገር ባይቻልም በማያቋርጥ ስልጠናና ልምምድ ብቁና ሁሌም ዝግጁ ሆኖ መገኘት አስፈላጊ በመሆኑ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የዚህ አይነቱን ስልጠና አዘጋጅቷል። በመሆኑም አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የሀገር መሪዎችን ፣ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ከአደጋ የመጠበቅ እንዲሁም የበረራ ደኅንነትን የማረጋገጥ ተልዕኮዎችን ለመፈጸም የሰው ኃይሉን በተከታታይ ስልጠና እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል። ሰልጣኞችም በስልጠና ወቅት በንድፈ ሃሳብ፡ በተግባርና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስልጠና ማግኘታቸው ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬታማ አፈፃፀም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።   የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት አቶ ወንድወሰን ካሳ በበኩላቸው የቪአይፒ ደኅንነት ጥበቃ መኮንኖች ከፍተኛ ደኅንነታዊ አንድምታ ያላቸውን ግለሰቦች ደኅንነት ለመጠበቅ ተገቢውን ዕውቀት ፣ ክህሎት፣ አስተሳሰብ እና ስነምግባር ሊጨብጡ ይገባል ብለዋል። እያንዳንዱ የቪአይፒ ደኅንነት ጥበቃ ስምሪት ሊያጋጥሙ ከሚችሉ እንዲሁም ከሚገመቱና ካልተጠበቁ ስጋቶች እና ጥቃቶች የሀገር መሪዎችን፣ ቁልፍ የመሰረት ልማት ተቋማትን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል የተሟላ ዕቅድ አዘጋጅቶ የመሰማራት ባህልን ማዳበር እንደሚገባ ገልጸዋል። በብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በንድፈ-ሃሳብና በተግባር የተሰጠውን ስልጠና የተከታተሉ ሰልጣኞችም ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት በተግባር ልምምድ ማሳየታቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መረጃ አመልክቷል።
ፖለቲካ
አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት እንዲፈረም ጠየቁ
Jun 1, 2023 77
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ጠየቁ ሚኒስትር ዴኤታው ዛሬ በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። አምባሳደር ምስጋኑ በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈረም የሚደረገው ዝግጅት እንዲፋጠን ጠይቀዋል። የሁለቱ አገራት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በሚጀመርበት ሁኔታ ዙሪያም ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከወዲሁም አስፈላጊ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት እና ለማቋቋም እየተደረገ ያለውን ጥረት የኩዌት መንግስት እንዲደግፍም አምባሳደር ምስጋኑ ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢ በበኩላቸው በሁለቱ ሃገራት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የኩዌት መንግስት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የኩዌት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባው እንዲጀመር አስፈላጊውን ጥረት እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።
ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 
Jun 1, 2023 97
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚጠበቅባቸውን ሚና በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ጋር በመተባበር ለአገር ውስጥና ለውጭ ጋዜጠኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና እየሰጠ ነው። ሥልጠናው መገናኛ ብዙኃን ጸጥታና ደኅንነት በማረጋገጥ እንዲሁም ድንበር ዘለል የጸጥታ ሥጋት በመከላከል ሚናቸውን ማጎልበት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ትኩረት አድርጓል ተብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው እንቅስቃሴ ዲፕሎማቶች ብቻ ሳይሆን ጋዜጠኞችም ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። በመሆኑም ጋዜጠኞች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ገልጸው በተለይም ደግሞ ትክክለኛ መረጃዎችን በማሰናዳት ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት።   የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ጀማላዲን መሃመድ በበኩላቸው ሥልጠናው ጋዜጠኞች በጸጥታ ጉዳዮች ያላቸውን ግንዛቤ ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል። በተለይም በግጭትና በፀጥታ ጉዳዮች ላይ ኃላፊነት በተሞላበት አኳኋን እንዲሰሩ እንዲሁም ትክክለኛና ሚዛናዊ ዘገባዎችን ለማቅረብ አስፈላጊውን እውቀትና ክህሎት ለማዳበር የሚረዳ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የኢጋድ አባል አገራት ድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ ሥጋቶችን ለመቅረፍ የአባላትን አቅም ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ጋዜጠኞች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እንደሚረዳ ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) የጸጥታና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ፤ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና በበርካታ ድንበር ዘለል የጸጥታና ደኅንነት ሥጋቶች ያሉበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም መገናኛ ብዙኃን በቀጠናው የሚያጋጥሙ የጸጥታ፣ ደኅንነትና ወንጀል ሥጋት በአግባቡና በትክክለኛው መንገድ በመገንዘብ ገጽታ የሚገነቡና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስከብሩ ሥራዎችን በትኩረት መሥራት አለባቸው ነው ያሉት። በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ደኅንት ማረጋገጥ ብዙኃኑን ያሳተፈ ሁለገብ ሥራን የሚጠይቅ በመሆኑ በዚህ ረገድ የመገናኛ ብዙኃን የድርሻቸውን ጉልህ ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተጠቁሟል። የመገናኛ ብዙኃን ግጭትን መከላከል ብቻ ሳይሆን በድህረ ግጭት የሰላም ግንባታ እንዲሁም ደግሞ ሰላም በዘላቂነት እንዲረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ነው ያሳሰቡት።            
አገራዊ ምክክሩ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት መደላድል የሚፈጥር ነው - የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች  
May 31, 2023 90
ድሬዳዋ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ):- አገራዊ የምክክር መድረኩ ብሔራዊ መግባባት በመፍጠርና አንድነትን በማጠናከር የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት መደላድል እንደሚፈጥር የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች ገለጹ። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአገራዊ የምክክር ሂደት ላይ አጀንዳ ለማሰባሰብ ስለሚከናወኑ ተግባራትና የውይይት ተሳታፊዎች ልየታን አስመልክቶ በድሬዳዋ ለሁለት ቀናት ያዘጋጀው ስልጠና ተጠናቋል ። በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች እንዳሉት በአገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው የምክክር መድረክ ብሔራዊ መግባባት የሚፈጥር ወሳኝ የሽግግር ምዕራፍ ነው። ከድሬዳዋ መምህራን ማህበር የመጡት መምህርት ሙሉካ ሁሴን ስልጠናው በቀጣይ በሚካሄደው አገራዊ ምክክር ተሳታፊዎችን የመለየት ሂደት ተአማኒነትና አሳታፊነትን ያሟላ ለማድረግ እንደሚያስችል ገልጸዋል። “በአገር ደረጃ የሚካሄደው የምክክር መድረክ በዜጎች መካከል መቀራረብ እና አንድነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ከፍታ ለማረጋገጥ ያስችላል” ብለዋል። አገራዊ የምክክር መድረክ አገራዊ መግባባት ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የድሬዳዋ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዮናስ በትሩ ናቸው። በሰከነ መንፈስ መወያየት ለአገር ዘላቂ ሰላምና እድገት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንና የጋራ ምክር ቤቱ በቀጣይ የሚካሄዱ የምክክር ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ ይሰራል ብለዋል። የድሬዳዋ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ጥምረት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አንድነት ዘነበ "ኢትዮያዊያን የሚያካሂዱት ምክክር አገራዊ አንድነትን ለማጠናከር መሰረት የሚጥል ነው" ብለዋል። የምክክር መድረኩ ኢትዮጵያዊያን በራሳቸው አጀንዳዎች ላይ መግባባት የሚፈጥሩበት ብቻ ሳይሆን አንድነትና አቅም መፍጠር የሚያስችላቸው መሆኑን አመልክተዋል።   የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር እንዳሉት ኮሚሽኑ በሚያከናውነው የተሳታፊዎች ልየታ የተለያዩ ተቋማት እና ባለድርሻ አካላት የሂደቱን ግልጸኝነት ፣አሳታፊነትና ተአማኒነት የመታዘብና የማረጋገጥ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። የምክክር መድረኩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጨምሮ ሁሉንም የሚያሳትፍ በመሆኑ ብሔራዊ መግባባት በመፍጠር ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። በሰከነ መንገድ በመወያየት የጋራ አገራዊ መግባባት በመፍጠር ኢትዮጵያን ለማሻገር እንደሚያስችል አመልክተዋል።  
ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየሰሩ እንደሚገኙ የአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሚኖሩ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ገለጹ
May 31, 2023 84
ደብረ ብርሃን ግንቦት 23 / 2015 (ኢዜአ):- አብሮነትን በማጠናከር የአካባቢያቸውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ እየሰሩ እንደሚገኙ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሚኖሩ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች አስታወቁ። በአማራ ክልል የአንጎላላ ጠራ ወረዳ እና በኦሮሚያ ክልል የቅንቢቢት ወረዳ ነዋሪዎች በአካባቢያቸው ዘላቂ ሰላምን ማስፈንና ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የጋራ ውይይት ዛሬ አካሄደዋል። ከአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አጎላላ ጠራ ወረዳ ተሳታፊ የሆኑት መላከ መዊዕ ቀሲስ ገዛኸኝ ኃይሉ እንደገለጹት፤ የአማራና የኦሮሞ ሕዝብ በአንድነት፣ በፍቅር እና በመተሳሰብ የሚኖር ነው። ለሕዝቡ ሰላምን፣ ፍቅርን፣ አንድነትንና መተሳሰብን መሰረት አድርገው በማስተማር የአካባቢያቸው ሰላም በዘላቂነት እንዲጠበቅ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ከኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቅንቢቢት ወረዳ የመጡት ቄስ ተሰማ በላቸው በበኩላቸው በሕዝቦች መካከል ፍቅርና ሰላም ጸንቶ እንዲዘልቅ ወጣቶችን እያስተማርን ነው ብለዋል። የሕዝቦች አብሮ የመኖር እሴት እንዲጎለብትና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በማስተማር የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።   ከቅንቢቢት ወረዳ የመጡት የአገር ሽማግሌ አቶ ተስፋዬ ግርማ በበኩላቸው በአካባቢው የሚኖሩ የኦሮሞ እና የአማራ ህዝቦች ከትውልድ ትውልድ የተሻገረ የጋራ ታሪክና እሴት እንዳላቸው አውስተዋል። "የብሔር ልዩነት ሳይገድበን አብረን የምንኖር ሕዝቦች በመሆናችን የጀመርነውን የጋራ እድገት፣ ልማትና ዘላቂ ሰላም የማረጋገጥ ጥረት አጠናከክረን እንቀጥላለን" ብለዋል። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት የአገር ሽማግሌ አቶ ተስፋዬ ሞገስ በበኩላቸው ከኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ ወረዳ ሕዝቦች ጋር በፍቅርና በሰላም የምንኖረው በመማከርና በመወያየት ነው ሲሉ ገልጸዋል። አለመግባባቶች ሲኖሩ የአገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ጋር በመመካከር እየፈቱ እንደሚገኝና በዚህም የአካባቢው ሰላም ተጠብቆ መቆየቱን ተናግረዋል። "የአካባቢያችንን ሰላም ለማደፍረስ የሚጥሩ ኃይሎችን እኩይ ሴራ ቀድሞ በማክሸፍ ሰላሙ ጽንቶ እንዲዘልቅ በጋራ የጀመርነው ውይይትና ምክክር ተጠናክሮ ይቀጥላል" ብለዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች ከአካባቢያቸው ባለፈ በአገር አቀፍ ደረጃ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ መንግስት የሚያደርገውን ጥረት በመደገፍ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።    
የሲዳማ ክልል የህዝብ አደረጃጀቶች የህዝብ ጥያቄዎች ለአገራዊ ምክክር መድረክ እንዲቀርቡ ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡ ገለጹ 
May 31, 2023 81
ሀዋሳ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ) የህዝብ ጥያቄዎች ለአገራዊ ምክክር መድረክ እንዲቀርቡ ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡ በአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በተባባሪነት የተለዩ የሲዳማ ክልል የህዝብ አደረጃጀቶች አስታወቁ። ኮሚሽኑ በተሳታፊ ልየታና አጀንዳ መረጣ ላይ ለሚሳተፉ ተባባሪ አካላት በሀዋሳ ከተማ ባዘጋጀው ስልጠና ላይ የተሳተፉ የሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የእድርና ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የኮሚሽኑ ስራ በስኬት እንዲጠናቀቅ የዜጎች ያልተቆጠበ ተሳትፎ ያስፈልጋል። በመሆኑም በምክክሩ የሚሳተፉ የህብረተሰብ ተወካዮችን የመምረጥ ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እንደሚወጡ ገልጸዋል። በሲዳማ ክልል ሴቶች ማህበር የሲቪክ ማህበረሰብ ተወካይ ወይዘሮ ዘውዲቱ ጥላሁን በአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለሚከናውነው ታላቅ ተልእኮ በተባባሪነት መመረጣቸው ከፍተኛ ሃላፊነት እንደሆነ ገልጸዋል። ይህን ሃላፊነት በአግባቡ በመወጣት እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ያሉ ሴቶች ድምጽ እንዲሰማ ለማድረግ የሴቶችን ተሳትፎ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በሰላም ማጣት የበለጠ ተጎጂ ከሚሆኑት ማህበረሰብ ክፍሎች ሴቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በሂደቱ ሴቶች በንቃት እንዲሳተፉ ለማስቻል እንሰራለን ብለዋል። የመልጋ ወረዳ አካል ጉዳተኞች ማህበር ሰብሳቢ አቶ ሃየሶ ሃሶ በበኩላቸው በብሄራዊ ምክክር ሂደቱ የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ እንዲኖር መደረጉ በርካታ ችግሮችን ለመቅረፍ ያስችላል ብለዋል።   በስልጠና መድረኩ ያገኙትን ግንዛቤ ተጠቅመው በምክክር መድረኩ ተገቢውን ሃሳብ ሊያንሸራሽሩ የሚችሉ ተወካዮችን በመምረጥ ከብሄራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ጋር እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመፍታት የሀገርን ህልውና ለማስቀጠል የብሄራዊ ምክክሩ አስፈላጊነት በዜጎች ቅቡልነት ያገኘ ነው ያሉት ደግሞ የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተወካይ አቶ ሃብተማርያም አብዩ ናቸው። የማያስማሙን ጉዳዮች ቢኖሩ እንኳን በአገር ሰላምና አንድነት ላይ ባለመደራደር የንግግር ባህልን ማሳደግና ከችግሩ ለመውጣት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በሀዋሳ ከተማ የመሀል ክፍለ ከተማ እድር ተወካይ አቶ መስፍን ዘውዴ በበኩላቸው አገራዊ ምክክሩ ለግጭት መንስኤ እየሆኑ ላሉ በርካታ ችግሮች መፍትሄ የሚሰጥ በመሆኑ ብርቱ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። እድሮች የተለያየ ህብረተሰብ ክፍል የሚሳተፍባቸው እንደመሆናቸው መጠን ለሀገር ጠቃሚ ሃሳቦችን ማመንጨት እንደሚችሉ አመልክተዋል። በመሆኑም የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ አካላትን በመምረጥ የህዝቡን ችግር በተገቢው የሚያሳይ አጀንዳ ለመምረጥ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ብሄራዊ ምክክር ኮሚሽን በሲዳማ ክልል በአጀንዳ ማሰባሰብና ምክክር ላይ የሚሳተፉ አባላትን ለሚመለምሉ ተባባሪ አካላት በሀዋሳ ስልጠና መስጠቱ ይታወሳል።
ብልፅግና ፓርቲ በሰጠው ጠንካራና ቅቡልነት ያለው አመራር የሀገረ መንግስት ግንባታን የሚያፋጥኑ ስራዎች ተከናውነዋል - የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ
May 31, 2023 108
አዲስ አበባ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ)፦ብልፅግና ፓርቲ በሰጠው ጠንካራና ቅቡልነት ያለው አመራር የሀገረ መንግስት ግንባታን የሚያፋጥኑ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳን አቶ አደም ፋራህ ገለጹ። ፓርቲው የተጀመሩ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ዲፕሎማሲያዊ ስራዎች በስኬት እንዲቀጥሉ የፓርቲውን አመራር የማጥራት፣ የማጠናከርና የመገንባት ስራ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ በቆየው መደበኛ ስብሰባ ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎችና ነገ የሚጀመረውን የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ በማስመልከት ለኢዜአ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በዲፕሎማሲያዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ገምግሞ የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል ብለዋል፡፡ በፖለቲካው ዘርፍ የጋራ መግባባት ያልተደረሰባቸው መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን በምክክር ኮሚሽኑ አማካኝነት በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመፍታት የተጀመረው ጥረት መልካም መሆኑ ተገምግሟል ነው ያሉት፡፡ የብልጽግና ፓርቲም ሁሉንም አሳታፊ ውይይት እንዲደረግ እና የጋራ ብሔራዊ መግባባት ላይ እንዲደረስ እንደ አንድ ፓርቲ የበኩሉን ሚና እንዲያበረክት አቅጣጫ መቀመጡን አንስተዋል፡፡ ፓርቲው በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ስርዓትን ለማንበር በርዕዮትና በፖሊሲ የሚለዩትን የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመንግስት መዋቅር ውስጥ በማሳተፍ የትብብር መንፈስ እንዲፈጠር አድርጓል፤ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ዘላቂና አወንታዊ ሰላም ለመፍጠር ለህዝብ ጥቅም የቆሙ ነፃና ገለልተኛ የጸጥታና ደህንነት እንዲሁም የዴሞክራሲ ተቋማትን በመገንባት አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ የትጥቅ ትግል ሲያካሂዱ ከነበሩ አካላት ጋር ዘመናዊና ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ያጣመረ ውይይት በማካሄድ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጥረት መደረጉ በስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በአዎንታዊነት እንደተገመገመ ጠቅሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የቡድንና የግል ፍላጎትን በኃይል ለማሳካት ያሰቡ ጽንፈኛ አካላት ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን እየፈተኑት ነው ያሉት አቶ አደም፤ ነፃነትን ለመጠቀም የሌሎችን ነፃነት ማክበር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የህግ የበላይነትንና ህገ መንግስታዊነትን ማረጋገጥ፣ የተሟላ ሀገራዊ ሰላምን ማፅናት፣ የፍትሕና ፀጥታ ተቋማትን ማጠናከር፣ የሁለም ኢትዮጵያውያን የወል እውነቶችን ገዥ ቦታ እንዲይዙ ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ ማስቀመጡን ተናግረዋል። ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ባለፉት 10 ወራት ፍትሐዊ ልማትን ከማረጋገጥ አንጻር አካታች ኢኮኖሚ እየተገነባ መሆኑን በውይይቱ እንደተመለከተም አብራርተዋል። የብዝኃ ዘርፍ የኢኮኖሚ ስርዓትን በማስቀጠል የተመዘገቡ ስኬቶች መኖራቸውን ገልጸው፤ በተለይም በስንዴ ምርታማነት የታየውን ውጤት በትልቅ ስኬት ማነሳቱን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ችግር በመፍታት፣ ምርታማነትን ለማሳደግና የገበያ ትስስር በመፍጠር አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ በገበታ ለሀገር እና ሌሎች ፕሮጀክቶች የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት መቻሉን እንዲሁም ከስራ ዕድል ፈጠራ አኳያ በዘጠኝ ወራት ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የዋጋ ንረትን ለማረጋገት፣ ኮንትሮባንድን ለመከላከል፣ በአምራችና ሸማቹ መካከል እሴት የማይጨምሩ የገበያ ሰንሰለቶችን ለመቀነስ ጠንካራ ርምጃዎች እንዲወሰዱ አቅጣጫ ማስቀመጡን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ አካታች የማህበራዊ ልማትን ለማጎልበት በትምህርት፣ በጤና እንዲሁም በወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይ አበረታች ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም በማህበራዊ መስክ ያሉ የትምህርት ጥራት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተጠቃሚነትን መሰረተ ያደረገ ሥነ ምግባራዊና ሀገር ውዳድ ትውልድ ግንባታ ይከናወናል ብለዋል፡፡ ትብብርና የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ የዲፕሎማሲ ስራዎች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰው፤ ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ በመስጠት የኢኮኖሚ ትስስር ፣ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲጠናከር የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። የሀገርን ክብር የማስጠበቅ አካሄዳችን ያልተመቻቸው አካላት የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ የፈጠሩብንን ጫና በመቋቋም የሀገር ሉዓላዊነታችንና የግዛት አንድነታችንን አስጠብቀን ቀጥለናል ብለዋል፡፡ ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ የመስጠት መርህ ውጤት በማስገኘቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ በቀጣይም ሚዛኑን የጠበቀ ሁሉን አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ አካሄድን በመከተል የፖሊሲ ነጻነታችንን የሚጋፉና ፍትሐዊ ተጠቃሚነታችንን እንዳናረጋገጥ የሚፈትኑ ጫናዎችን የመመከትና ወዳጅነትን የማስፋት ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ መቀመጡን አንስተዋል። ብልጽግና ፓርቲ የተጀመሩ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ዲፕሎማሲያዊ ስራዎች በስኬት እንዲቀጥሉ የፓርቲውን አመራር የማጥራት፣ የማጠናከርና የመገንባት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ ፈጠራና ፍጥነትን ተጠቅሞ የፓርቲውን አደረጃጀት ማጠናከር፣ የውስጠ ፓርቲ አንድነትና ዴሞክራሲን ማጎልበት፣ ብሎም በምርጫ ወቅት ለህዝብ የተገባውን ቃል በውጤታማነት መፈጸም የቀጣይ ትኩረት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ለዘላቂ ሰላም መስፈን የድርሻቸውን እንደሚወጡ የጌዴኦ ዞን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ
May 31, 2023 84
ዲላ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ) ለዘላቂ ሰላም መስፈን የድርሻቸውን እንደሚወጡ የጌዴኦ ዞን የቤተ እምነት መሪዎችና የባህል አባቶች አስታወቁ። የሰላም እሴቶችን ለማጽናትና ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልን ዓላማው ያደረገ የሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ የሚመክር መድረክ ዛሬ በዲላ ከተማ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የቤተ እምነት መሪዎች፣ የባህልና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ አስተዳደር የስራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል በኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን የልማት ካውንስል ዳይሬክተር መጋቢ ቦካኮ ዱጉማ እንዳሉት ስለ ሰላም መስራት የቤተ እምነቶች ተቀዳሚ ተልዕኮ ነው። "ልጆቻችንን ስናሳደግ ጥላቻና በደል እያስተማርን ሳይሆን ለሀገርና ለወገን የሚበጀውን ስለ ፍቅር፣ ሰላም፣ አብሮነትና አንድነትን በመመገብ ሊሆን ይገባል" ብለዋል። በተለይም ታሪክን ለአገር ግንባታና ለትውልድ ትምህርት መውሰድ እንጂ የጠብና የግጭት ምንጭ አድርገን መተረክ እንደማይገባ አስገንዝበዋል። የቋንቋና የሃይማኖት ልዩነቶች ውበትና ጸጋዎች መሆናቸውን ተረድተን ከአክራሪነትና የኔ ብቻ ከሚል ጽንፈኝነት ይልቅ ለሰላምና ለመቻቻል ቅድሚያ መስጠት ይገባል ብለዋል። በተለይም በሀገራችን የመጣውን የሰላም አየር ዘላቂና ወንድማማችነትን ያጎለበተ እንዲሆን ግንባር ቀደም ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል። የጌዴኦ ብሔር ባህላዊ የባሌ አስተዳደር መሪ አባ ገዳ ቢፎሚ ዋቆ በበኩላቸው በሀገራችን የሚገኙ በርካታ ባህሎች ለሰላም ግንባታ ጠቃሚ እሴቶች ያሉ ቢሆንም በአግባቡ ከመጠቀም አንጸር ውስንነቶች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። የባህል አባቶችና የቤተ እምነት መሪዎች "ግጭትን ለማስቀረት የምናደርገውን ጥረት ያክል ያገኝነውን የሰላም አየር ዘላቂ ለማድረግም ልንሰራና ልንጥር ይገባል" ብለዋል። በተለይም በውስጣችን ለግጭት መነሻ የሆኑ አስተሳሰቦችን በውይይት የመፍታት ባህላችንን በማሳደግ ለትውልዱም ሆነ ለሀገራችን የፖለቲካ ስርዓቱ ምሳሌ መሆን ይጠበቅብናል ሲሉም ተናግረዋል። የሰላም እሴቶችን ማስተዋወቅና ማስተማር ለዘላቂ ሰላም መሰረት መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የጌዴኦ ዞን የሃይማኖት ተቋማት ካውንስል ሰብሳቢ ቄስ አያሌው ሙርቲ ናቸው። የተለያዩ ሃይማኖት ተከታዮች ከጥላቻና መገፋፋት ይልቅ ወንድማማችነትንና ወዳጅነትን እንዲያስቀድሙ የጋራ እሴቶች ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ምስጋና ዋቀዮ በበኩላቸው በሀገራችን የመጣውን የሰላም ሁኔታ ሊያሻክሩ የሚችሉ ጽንፈኝነትን በጋራ መከላከል ይገባል ብለዋል። በተለይም በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ጥላቻና ግጭትን የሚሰብኩ የፖለቲካ ነጋዴዎች ተቀባይነት እንዳያገኙና ትውልዱን በሰላም እሴቶች በመገንባቱ ረገድ የቤተ እምነት መሪዎችና የባህል አባቶች ድርሻቸው የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአንጻሩ ወንድማማችነትን የሚያጎለብቱ መድረኮችን በማጠናከር ሀገራዊ ሰላማችንን ዘላቂ በማድረጉ ረገድ የድርሻቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተስፋጽዮን ዳካ በበኩላቸው በህብረተሰቡ ዘንድ መግባባት እና መተማመን በመፍጠር ፍፁም የሆነ ሰላም ማምጣት እንደሚቻል አመላክተዋል። ከግጭት የሚያተርፉ አካላት መቼውንም ጊዜ ለሰላም ፍላጎት የሌላቸው በመሆኑ የጋራ ትግል ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል። መሰል የሰላም ግንባታ ስራዎች ደግሞ ወጣቱን በይበልጥ ተሳታፊ ማድረግ እንዳለበት ጠቅሰው፤ በተለይ አባቶች ትክክለኛውን ታሪክ ለትውልድ በማስተላለፍ ለሰላም ግንባታ በሚደረገው ጥረት አጋዥ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።    
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለእጀባ ለበረራ ደህንነትና ቁልፍ የመሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ የሰው ኃይሉን በተከታታይ ስልጠናዎች እያበቃ መሆኑ ተገለጸ
May 31, 2023 82
አዲስ አበባ ግንቦት 23/2015(ኢዜአ)፦የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የሀገር መሪዎችን፣ ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ከአደጋ የመጠበቅና የበረራ ደኅንነትን የማረጋገጥ ተልዕኮውን በብቃት ለመፈጸም የሰው ኃይሉን በተከታታይ ስልጠናዎች እያበቃ መሆኑን ገለጸ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለሪፐብሊካን ጋርድና ለአገልግሎት መስሪያ ቤቱ እጀባ ፣ለበረራ ደኅንነት መኮንኖችና አመራሮች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን አስመርቋል። አገልግሎቱ ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መረጃ እንዳመለከተው በትብብርና በአጋርነት አብረውት ከሚሰሩ የውጭ መረጃና ደኅንነት ተቋማት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ይህ ስልጠና በዋናነት በቪአይፒ ደኅንነት ጥበቃ፣ በፈንጂ ምህንድስና ፣በድሮን አጠቃቀም ቅየሳና የአደጋ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ያተኮረ ነው። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ በምረቃው ላይ እንደገለጹት አደጋ መቼና እንዴት እንደሚከሰት በእርግጠኝነት መናገር ባይቻልም በማያቋርጥ ስልጠናና ልምምድ ብቁና ሁሌም ዝግጁ ሆኖ መገኘት አስፈላጊ በመሆኑ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የዚህ አይነቱን ስልጠና አዘጋጅቷል። በመሆኑም አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የሀገር መሪዎችን ፣ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ከአደጋ የመጠበቅ እንዲሁም የበረራ ደኅንነትን የማረጋገጥ ተልዕኮዎችን ለመፈጸም የሰው ኃይሉን በተከታታይ ስልጠና እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል። ሰልጣኞችም በስልጠና ወቅት በንድፈ ሃሳብ፡ በተግባርና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስልጠና ማግኘታቸው ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬታማ አፈፃፀም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።   የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት አቶ ወንድወሰን ካሳ በበኩላቸው የቪአይፒ ደኅንነት ጥበቃ መኮንኖች ከፍተኛ ደኅንነታዊ አንድምታ ያላቸውን ግለሰቦች ደኅንነት ለመጠበቅ ተገቢውን ዕውቀት ፣ ክህሎት፣ አስተሳሰብ እና ስነምግባር ሊጨብጡ ይገባል ብለዋል። እያንዳንዱ የቪአይፒ ደኅንነት ጥበቃ ስምሪት ሊያጋጥሙ ከሚችሉ እንዲሁም ከሚገመቱና ካልተጠበቁ ስጋቶች እና ጥቃቶች የሀገር መሪዎችን፣ ቁልፍ የመሰረት ልማት ተቋማትን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል የተሟላ ዕቅድ አዘጋጅቶ የመሰማራት ባህልን ማዳበር እንደሚገባ ገልጸዋል። በብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በንድፈ-ሃሳብና በተግባር የተሰጠውን ስልጠና የተከታተሉ ሰልጣኞችም ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት በተግባር ልምምድ ማሳየታቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መረጃ አመልክቷል።
ማህበራዊ
በኢትዮጵያ የኪነጥበብ ኢንዱስትሪው ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያለውን ሚና ለማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር ይገባል-የኪነጥበብ ባለሙያዎች
Jun 1, 2023 52
አዲስ አበባ ግንቦት 24/ 2015 (ኢዜአ) በኢትዮጵያ የኪነ ጥበብ ኢንዱስትሪው ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያለውን ሚና ለማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የኪነ-ጥበብና ስነ-ጥበብ ፈጠራን ለማሳደግ የሚያስችል የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በውይይቱ በኪነጥበብና ስነ ጥበብ የስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ የመወያያ የመነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የማኑፋከቸሪንግ ልማት ባለሙያ አቶ በኃይሉ ዓለማየሁ፤ የጥበብ ኢንዱስትሪ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገትና ለዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ረገድ እምቅ አቅም ያለው ዘርፍ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ፈርጀ ብዙ የባህል ኪነጥበብ ቢኖራትም በሚፈለገው ልክ ባለማደጉ ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያለው አበርክቶ አነስተኛ ሆኖ መቆየቱን ጠቅሰዋል። ሆኖም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዘርፉ እየተነቃቃ መምጣቱን በማንሳት በዚህም በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ያለው ድርሻ እየጨመረ መምጣቱን ነው የገለጹት። አቶ በኃይሉ የናይጄሪያ የፊልምና የሙዚቃ ኢንዱስትሪ በስራ እድል ፈጠራ ያለውን ትልቅ ሚና በተሞክሮነት ጠቅሰው፤ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት ከነዳጅ ቀጥሎ ትልቁ የገቢ ምንጭ መሆኑን አስረድተዋል። ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ በመማር የኢትዮጵያን የኪነጥበብ ኢንዱስትሪ በማጎልበት ለሀገር ልማትና ለዜጎች ተጠቃሚነት ጉልህ አስተዋፅኦ እንዲያበረክት በቅንጅት መስራት ተገቢ መሆኑን አንስተዋል። የጥበብ ስራዎች ቅጅና ተዛማጅ መብቶች ዙሪያ የመወያያ ሀሳብ ያቀረቡት የሰዋሰው መልቲ ሚዲያ ጥናትና ምርምር ከፍተኛ ባለሙያ ታደሰ ኃይሉ በበኩላቸው፤ ሀገሪቱ ያላትን ዘርፈ ብዙ ባህልና እውቀቶች ለማሳደግና ተጠቃሚ ለመሆን የቅጅና ተዛማጅ መብቶች መከበር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይ ፈጠራን ለማሳደግና የሀገርን የቅጂ መብት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣንን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ነው ያመለከቱት። የሙዚቃ ባለሙያው ዳዊት ይፍሩ በበኩሉ፤ በነባርና አዳዲስ የኪነጥበብ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራቸው የቅጂ መብት ስጋቶች እንዳሉ በመጠቆም፤ አዳዲስና የተሻሉ የኪነጥበብ ፈጠራ ስራዎችን ለማውጣት የቅጂና ተዛማጅ መብቶችን ማረጋገጥ ላይ ላይ በትኩረት እንዲሰራ ጠይቋል። በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የዕደ ጥበብ ልማትና ገበያ ትስስር ማስፋፊያ ስራ አስፈጻሚ አቶ ነጋሽ በድሩ፤ መንግስት የኪነጥበብ ዘርፉን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሚና ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል። የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አወቀ ዘመነ፤ በኢኮኖሚ ያደጉ ሀገራት ለአዕምሮዊ ሃብት ጥበቃ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጡ ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያም ያልተነካውን የባህልና የጥበብ ዘርፍ ለማሳደግ በቁርጠኝነት መስራት ከሁሉም የሚጠበቅ ኃላፊነት መሆኑን ገልጸዋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በክረምቱ ከ50 ሺህ በላይ ወጣቶችን ያሳተፈ የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች ይከናወናሉ- ቢሮው
Jun 1, 2023 55
አሶሳ ግንቦት 24 / 2015(ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመጪው ክረምት ከ50 ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች እንደሚከናወኑ የክልሉ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ፡፡ በክልሉ የሻንጉል በጎ አድራጎት ማህበር በበኩሉ፤ ባለፉት ወራት ያከወናቸውን በጎ ተግባራት በመጪው ክረምትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡ የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ ሃጂራ ኢብራሂም ለኢዜአ እንዳሉት፤ ከመጪው ሐምሌ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ወራት የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች ለማከናወን አቅደዋል። በእቅዳቸው መሰረት በግል እና በማህበር የተደራጁ ከ50 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ተሳታፊ እንደሚሆኑ አስታውቀዋል፡፡ በበጎ ፈቃድ ስራ ክልሉን ብሎም የሃገሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት የሚከናወኑ ስራዎች መለየታቸውን ጠቁመዋል፡፡ ከመካከላቸውም ባለፉት ዓመታት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር በክልሉ አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚካሄድ ችግኝ ተከላና እንክብካቤ ዋነኛው እንደሆነ ወይዘሮ ሃጂራ ጠቅሰዋል፡፡ እንዲሁም አቅመ ደካሞችን የመርዳት ፣ የክረምት ትምህርት ማጠናከሪያ፣ የአካባቢ ጽዳትና ህገወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከል ከሚከናወኑት ተግባራት መካከል እንደሚገኙበት አመላክተዋል፡፡ በበጎ ፈቃድ ስራው የሚሳተፉ ወጣቶች በተጨማሪ በሚያከናውኗቸው ስራዎች ህብረተሰቡን ከመደገፍ ባሻገር የህይወት ተሞክሮዎች እንደሚቀስሙበት ጠቁመዋል፡፡ ባለፈው የበጋ ወቅት በተለይም ወጣቶች ከጸጥታ አስከባሪዎች ጎን በመቆም ለክልሉ ሠላም መመለስ ያደረጉት አስተዋጽኦ የሚበረታቱ መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ ሆኖም የወጣቶች ማህበራትን ከመደገፍ ጀምሮ የተደረው ጥረት አነስተኛ መሆኑን አመልክተው፤ ይህም በበጋው የበጎ ፈቃድ ስራ የቢሮው ዋነኛ ውስንነት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ውስንነቶችን ለማስተካከል በክረምቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ወይዘሮ ሃጂራ ገልጸዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሚገኙ የበጎ አድራት ወጣቶች ማህበራት መካከል 14 አባላትን የቀፈው የሻንጉል በጎ አድራጎት ማህበር አንዱ ነው፡፡   ማህበሩ ለትርፍ ያልተቋቋመና ዓላማው የተጎዱ ወገኖችን በመርዳት የሃገር ገጽታ መገንባት መሆኑን የማህበሩ ስራ አስኪያጅ ወጣት ፌኔት አያና ተናግራለች፡፡ በክልሉ በርካታ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ወገኖች አሉ ያለችው ወጣቷ፤ ከህብረተሰቡ የድጋፍ ገንዘብ በማሰባሰብ ለችግረኛ ወገኖች አነስተኛ መኖሪያ ቤት አሰርተው በመስጠት ባለፉት ወራት ካከናወኗቸው ተግባራት መካከል መሆኑን አስረድታለች፡፡ በመጪው ክረምትም ይኸው የበጎ ተግባር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል ወጣቷ ገልጻለች፡፡ የማህበሩ አባል ወጣት ወይንእሸት ደሳለኝ በሰጠችው አስተያየት፤ ለበጎ ፈቃድ ስራው የምናውለውን ገንዘብና ሌሎች የቁሳቁስ ድጋፎችን ከህብረተሰቡ ለማሰባሰብ ማህበራዊ ሚዲያን እየተጠቀምንበት ነው ብላለች፡፡ በበጎ ፈቃደኝነት የሚከናወኑ ተግባራት በምንም የማይተመን የህሊና እርካታ የሚሰጥ እንደሆነም ወጣቷ ለኢዜአ ገልጻለች፡፡ በሻንጉል በጎ አድራጎት ማህበር ወጣቶች የበጎ ፈቃድ የወደቀ ቤታቸው ተጠግኖ ለአገልግሎት መብቃቱን የተናገሩት ደግሞ አቶ ብርሃኑ ኪሮስ የተባሉ የአሶሳ ከተማ ነዋሪ ናቸው። በተደረገላቸው ድጋፍ ደስተኛ እንደሆኑና ለዚህም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፈው ዓመት 215 ሺህ 432 ሰዎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ከአራት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የበጎ ፈቃድ ስራዎች መከናወናቸውን ከቢሮው የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡  
የኢዜአ አመራርና ሠራተኞች ለ12ኛ ጊዜ ደም ለገሱ
Jun 1, 2023 66
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት /ኢዜአ/ አመራርና ሠራተኞች ለ12ኛ ጊዜ ደም ለገሱ። "በደም እጦት ሰው መሞት የለበትም" የሚለውን የዓለም ጤና ድርጅት መርህ ተግባራዊ ለማድረግ በተለያዩ አገሮች ዜጎቻቸው ደም መለገስን ባህል አድርገው ቀጥለዋል። በዚህ ተግባር አንዳንድ አገሮች ስኬታማ ሲሆኑ ሌሎች ደግሞ የድርጅቱን መርህ ለመተግበር በጥረት ላይ ይገኛሉ። በአንድ አገር ሰው በደም እጦት እንዳይሞት ከአጠቃላይ የሕዝብ ቁጥር 1 በመቶ ደም መስጠት እንዳለበት ይታመናል። በኢትዮጵያ በደም እጦት ሰዎች እንዳይሞቱ ለማስቻል በየሦስት ወሩ ከ1 ሚሊየን በላይ ሰዎች ደም መለገስ ይጠበቅባቸዋል። እስካሁን ባለው ሂደት ግን የደም ለጋሾች ቁጥር ከግማሽ ሚሊየን ያነሰ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሠራተኞች የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት በተለያዩ ጊዜያት የደም ልገሳ በማድረግ የላቀ አስተዋጽዖ እያበረከቱ ይገኛሉ። በመሆኑም የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች በዛሬው እለት ለ12ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሃ-ግብር አካሂደዋል።   ከደም ለጋሾቹ መካከል ጋዜጠኛ በሀብቱ ተሰማ በተደጋጋሚ ልገሳ ያደረገ ሲሆን፤ የእናቶችና ህፃናትን ሕይወት ለመታደግ አስተዋጽዖ በማድረጌ ከፍተኛ ደስታ ይሰማኛል ብሏል። የሰዎችን ሕይወት ለመታደግ ሁሉም የደም ልገሳን ባህል በማድረግ ለሰብአዊነት እንዲተጋ መልዕክቱን አስተላልፏል።   ሌላው ደም ለጋሽ ጋዜጠኛ ሚኪያስ ጎቡ፤ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚደርሱ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የሚሰጠውን ምላሽ የሚያግዝ መሆኑን ገልጿል። ደም በመለገሱ መደሰቱንም ገልፆ፤ ማንኛውም ጤነኛ ሰው በየሦስት ወሩ ደም በመለገስ በደም እጦት ሕይወታቸው የሚያልፍ ወገኖችን መታደግ አለበት ብሏል።   ሌላኛዋ የተቋሙ ሠራተኛ የንጉስ ውቤ፤ እስካሁን በተደረጉት የደም ልገሳ መርሃ-ግብሮች መሳተፋቸውን ጠቅሰው፤ በዛሬው እለትም ደም በመለገሳቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።   በኢዜአ የሴቶች እና ባለብዙ ዘርፍ ዳይሬክተርና የፕሮግራሙ አስተባባሪ ታደለች ቦጋለ፤ የተቋሙ ሰራተኞች በየሶሰት ወሩ ደም መስጠትን ባህል አድርገው መቀጠላቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም በተለያዩ ምክንያቶች ደም የሚሹ ወገኖች ሁላችንም ደማችንን በመለገስ ህይወታቸውን ማትረፍ አለብን ብለዋል። የተቋሙ ሰራተኞች በተከታታይ የደም ልገሳ መርሃ ግብር በማከናወን ባህል አድርገው የቀጠሉ ሲሆን በዛሬው እለትም ለ12ኛ ጊዜ ደማቸውን ለግሰዋል።  
አገር አቀፍ የሥነ-ምግባርና የሙስና መከላከል ረቂቅ ፖሊሲ ተዘጋጅቷል - የፌዴራል ሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን
Jun 1, 2023 52
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፦ አገር አቀፍ የሥነ-ምግባርና የሙስና መከላከል ረቂቅፖሊሲ መዘጋጀቱን የፌዴራል ሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር እሸቴ አስፋው ገለጹ። ኮሚሽኑ ፖሊሲውን በሚመለከትና አሰራሩን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ እየሰራ ያለውን ሥራ በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል።   የፌዴራል ሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር እሸቴ አስፋው በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ሙስና በአገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን አንስተዋል። የሙስና ወንጀል በዜጎች የዕለት ዕለት እንቅስቃሴ ላይ እያደረሰ ያለው አሉታዊ ጫና ማኅበራዊ ቀውስ እያስከተለ ከመሆኑ ባሻገር አገራዊ ሥጋት ሆኗል ነው ያሉት። በመሆኑም በአገር አቀፍ ደረጃ የጸረ ሙስና ትግሉን ስኬታማ ለማድረግ የሚያስችል አገር አቀፍ የሥነ-ምግባርና የሙስና መከላከል ረቂቅ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል። ረቂቅ ፖሊሲው በጥናት ላይ የተመሰረተና የሌሎች አገራትን ተሞክሮ ከግምት ያስገባ እንዲሁም የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ ረቂቅ ፖሊሲ ነው ብለዋል። ፖሊሲውን በሚመለከት የክልልና የከተማ መስተዳደር ተጠሪ ተቋማት፣ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። ከዚህ ጎን ለጎን በውይይቱ በሙስና ዙሪያ የሚከናወኑ ተግባራትን በቴክኖሎጂ አሰራር ለመደገፍ የተከናወኑ ተግባራትም ውይይት እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመዋል። ለዚህም የሃብት ምዝገባን ጨምሮ የሙስና ወንጀል ጥቆማ የሚከናወንበት ቴክኖሎጂን የማስተዋወቅና በቀጣይ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር መዘጋጀቱንም አክለዋል። ውይይቱ ዛሬን ጨመሮ ለሁለት ቀናት የሚካሄድ ይሆናል።    
ኢኮኖሚ
ዩኒቨርሲቲዎች አገር በቀል እውቀቶችን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማስተሳሰር ለአገር ግንባታ ማዋል እንዳለባቸው ተገለጸ
Jun 1, 2023 52
ደብረ ብርሃን ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገር በቀል እውቀቶችን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማስተሳሰር ለአገር ኢኮኖሚ ግንባታ እና ለችግሮች መፍቻ ማዋል እንደሚገባ ተጠቆመ። በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ "የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሳምንት ቀን" በተለያዩ ዝግጅቶች በመከበር ላይ ነው። የኢትዮጵያ ባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ካሳሁን ተስፋዬ እንዳሉት፣ የአገር ኢኮኖሚን ለመገንባት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በምርምር የታገዘ ድጋፍ ማድረግ አለባቸው። ተቋማቸው የአገር ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ እንዲቀመጥ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በምርምር እንዲወጡና ለተጠቃሚዎች እንዲደርሱ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።   ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በሲዳማ ክልል ይርጋለም ከተማ የቡና ገለባን ወደ ማዳበሪያ ለመቀየር ያከናወነው ስራ ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ ቴክኖሎጂውን ለአርሶ አደሮች እንዲሸጋጋር መደረጉን ተናግረዋል። እንዲሁም የቲማቲም በሽታን በመከላከል የዘርፉን ምርታማት ለማሳደግ ከኬሚካል ነጻ የሆነ የተባይ መከላከያ መድሀኒት ተቋሙ በምርምር ማውጣቱን ነው የገለጹት። ከእዚህ በተጨማሪ የማሽላ ጥንቅሽ ዝርያን ለፋርማሲዩቲካልና ለምግብነት አገልግሎት ለማዋል ከመልካሳ ግብርና ምርምር ጋር ውጤታማ ስራ መሰራቱን ነው ዶክተር ካሳሁን የተናገሩት። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገር በቀል እውቀቶችን ከመጠበቅ ባለፈ ከአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማስተሳሰር አገራዊ ችግሮችን ለመፍታትና ለኢኮኖሚ ግንባታ ማዋል እንዳለባቸው አሳስበው ተቋሙ ለዚሁ ስራ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ጥናትና ምርምር የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር አዝመራ አየሁ በበኩላቸው፣ በዩኒቨርሲቲው ችግር ፈች የምርምር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።   ለዚህም በግብርናው ዘርፍ የተቀናጀ የአሳ እርባታ፣የኮምፖስት ዝግጅት እንዲሁም የአንኮበር የመድኃኒት እጽዋት ምርምሮች ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን በማሳየነት ጠቅሰዋል። ከኢንዱስትሪ ባለሀብቶች ጋር በመቀናጀት የኢንዱስትሪ ዩኒቨርሲቲ ትስስርን ለማጠናከር ጅምር ሥራዎች እንዳሉም አንስተዋል። እንደ አገር ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ዩኒቨርሲቲው ብቁ እና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል በማፍራት የድርሻውን እየተወጣ ነው መሆኑን ነው ምክትል ፕሬዝዳንቱ የተናገሩት። በዚሁ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሳምንት ቀን የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ተማሪዎች እንዲሁም አምራች ኢንዱስትሪዎችና ተመራማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።  
በሐረሪ ክልል የስራ እድል ለመፍጠርና የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት አመራሩ ቅንጅቱን አጠናክሮ መስራት እንዳለበት ተጠቆመ
Jun 1, 2023 49
ሐረር፣ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ) በሐረሪ ክልል የስራ እድል ለመፍጠርና የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት አመራሩ ቅንጅቱን አጠናክሮ ሊሰራ እንደሚገባ የብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልጀባር መሀመድ አስገነዘቡ። በክልሉ በምግብና ሸቀጦች ላይ የሚታየውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋትና ለዜጎች የስራ እድል መፍጠር ለማስቻል ያለመ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልጀባር መሀመድ እንደተናገሩት፤ በክልሉ የሸቀጥ ዋጋን ለማረጋጋት የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ፓርቲው በክልሉ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የተካተቱበት ግብረ ሃይል በማቋቋም የግብርና ምርቶችን ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በማምጣት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲዳረስ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በክልሉ ዋጋን ለማረጋጋት እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች አበረታች ቢሆኑም ቀጣይነት ያለው ስራ ማከናወን ተገቢ መሆኑን አስምረውበታል። በተለይ የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት በሚከናወኑ ስራዎች ላይ ማነቆ የሆኑ ተግዳሮቶችን ከመቅረፍ አንጻር አሁንም ክፍተት እንደሚታይ ጠቁመው፤ ችግሮቹን ለመቅረፍ አመራሩ ተቀናጅቶ መስራት አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል። አቶ አብዱልጀባር አክለውም፤ በክልሉ በቀጣይ አምስት ወራት በሚከናወነው ንቅናቄ አመራሩ ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጎልበት ወጣቱን የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል ብለዋል። በክልሉ ለስራ እድል ማነቆ የሆኑ አሰራሮችን በባለቤትነት በመቅረፍና የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። በክልሉ በሚገኙ ገጠር ወረዳዎች ላይ ወጣቱን በግብርና ዘርፍ በማሰማራት አምራችነት እንዲጎለብት የማድረግ ስራ መጠናከር እንዳለበትም ጠቁመዋል። የክልሉ ንግድ ልማት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ቡሽራ አልይ በበኩላቸው በክልሉ አነስተኛና ቋሚ ገቢ ያላቸው ዜጎች ላይ የሚታየውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ዘንድሮ በቅዳሜ ገበያ 30 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው የግብርና ምርት ግብይት እንዲከናወን ተደርጓል ብለዋል። በተጨማሪም 696 ሺህ ሊትር ዘይት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲከፋፈል መደረጉን ተናግረዋል። ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 1 ሺህ 452 ህገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል። በቀጣይ አምስት ወራትም በክልሉ ነጻ የምርት ዝውውርን በማጎልበት፣ በቂ የምርትና የሸቀጥ አቅርቦትን በማሳደግ፣ ህገ ወጥ ነጋዴዎችንና ደላላዎችን በመከላከል ዋጋ የማረጋጋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል። የክልሉ የኢንተርፕራይዞች ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አሪፍ መሀመድ በቀጣይ አምስት ወራት ከሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር በተቀናጀ ለዜጎች የስራ እድል የመፍጠር ስራ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። በቀጣይ አምስት ወራት በግብርናና አረንጓዴ አሻራ ልማት 2 ሺህ 600 ወጣቶችን ስራ ለማስያዝ መታቀዱን ተናግረዋል።
በሀዋሳና ጅማ አዲስ የደረቅ ወደብ ተርሚናል ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል - የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ
Jun 1, 2023 58
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፦በሀዋሳና በጅማ አዲስ የደረቅ ወደብ ተርሚናል ግንባታ ሂደቶች በቅርቡ የሚጀመሩ መሆኑን የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ድርጅት ገለጸ። የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የወደብና ተርሚናል ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ምሕረተአብ ተክሉ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ተቋሙ በአገሪቱ ለገቢና ወጪ ጭነቶች የሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ነው። የወጪና ገቢ ንግድ ፍሰት የሚመጥንና ሊያስተናግድ የሚችል የሎጂስቲክስ አቅርቦትና የደረቅ ወደብ ተርሚናል ማስፋፊያ እንዲሁም አዳዲስ የደረቅ ወደብ ግንባታ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይም ተጨማሪ የደረቅ ወደብ ግንባታ በየጊዜው እየጨመረ ሲሄድ የወጪ ገቢ ንግድ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ባለሃብቶችን ለማበረታታትና ተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅም ለመፍጠር የላቀ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል። በመሆኑም ተቋሙ በሀዋሳና በጅማ ሁለት አዳዲስ የደረቅ ወደብ ተርሚናሎች ግንባታን በጥቂት ወራት ውስጥ እንደሚጀምር ጠቅሰው፤ ለፕሮጀክቶቹ ቅድመ ግንባታ ለእያንዳንዳቸው 150 ሚሊዮን ብር በጀት ተይዞላቸዋል ነው ያሉት። ይህም በጀት ለወሰን ማስከበር፣ ማማዎችን ለመገንባት፣ ጊዜያዊ ቢሮዎችን ለማቋቋምና ሌሎች ተያያዥ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ሥራዎችን ለማከናወን እንደሚውል ጠቁመዋል። የቀጣይ ምዕራፍ ግንባታም የቢዝነስ ጥናቱን ተከትሎ ተጨማሪ በጀት በመመደብ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በተለይም የሀዋሳ ደረቅ ወደብ ግንባታ ከአምስት ዓመታት በፊት የተጀመረ መሆኑን አንስተው፤ ከመሬት አቅርቦት ጋር ተያይዞ ለረዥም ጊዜ መጓተቱን አስረድተዋል። ይህም ሆኖ አሁን ላይ እነዚህ ችግሮች እልባት አግኝተው የግንባታ ሥራ ለመጀመር የቢዝነስ ጥናቱ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በ3 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፈው ይኸው የሀዋሳ የደረቅ ወደብ በቀጣዩ በጀት ዓመት መጀመሪያ የግንባታ ሥራው ይጀመራል ብለዋል። በሃያ ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፈውን የጅማ ደረቅ ወደብ ተርሚናል ግንባታ ለመጀመር የመሬት አቅርቦት በአጭር ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁን ገልጸዋል። የግንባታ ዲዛይኑ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ዓመት መጀመሪያ ግንባታው እንደሚጀመር ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በስምንት የደረቅ ወደቦች ላይ በደንበኞች ፍላጎትና የሎጂስቲክስ አገልግሎቱን ለማሳለጥ በሚያስችል መልኩ የማስፋፊያ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ተቋሙ የሚያከናውናቸው የአዳዲስ ደረቅ ወደብ ግንባታዎችና የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች የአገሪቱን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማሳለጥ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ነው ያስረዱት።
በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ ውጤታማ የልማት ሥራዎችን በማስቀጠል የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሁሉም ጥረት ሊታከልበት ይገባል- ዶክተር ፍጹም አሰፋ
Jun 1, 2023 107
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ) በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ ውጤታማ የልማት ሥራዎችን በማስቀጠል የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሁሉም ጥረት ሊታከልበት ይገባል ሲሉ የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽን ሚያዝያ 29 ቀን 2015 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተመርቆ ለጎብኝዎች ክፍት መሆኑ ይታወቃል። በዚህም እስካሁን የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ሌሎችም ኤግዚቢሽኑን ጎብኝተዋል። በዛሬው እለትም የፌደራልና የክልል የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አውደ-ርዕዩን ጎብኝተዋል።   ከጉብኝቱ ተሳታፊዎች መካከል የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ዶክተር ፍጹም አሰፋ፣ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና ሌሎችም የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ከጉብኝቱ ጎን ለጎንም በሲዳማ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች የተዘጋጀውና በሌማት ትሩፋት የተገኙ ውጤቶችን የሚያስቃኝ አውደ-ርዕይን በሳይንስ ሙዚየም መርቀው ከፍተዋል። በሁለቱ ክልሎች የተዘጋጀው አውደ-ርዕይ ላይ የዓሳ፣ የማር፤ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የቅመማቅመም፣ የእንስሳት ተዋጽዖዎችን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ውጤቶች ለዕይታ ቀርበዋል። በኢትዮጵያ በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴና የአረንጓዴ ልማት መርሃ-ግብሮች ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገልጸዋል። በኩታገጠም የአስተራረስ ዘዴ እያደገ የመጣው የግብርና ሜካናይዜሽን ጋር ተዳምሮ ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ መሆኗን በተግባር እያየን ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ለዘመናት ከውጭ ይገባ የነበረውን ምርት በማስቀረት ለውጭ ገበያ ጭምር ማቅረቧ የውጤታማነቱ ሁነኛ ማሳያ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በግብርናው ዘርፍ የተጀመሩ ውጤታማ የልማት ሥራዎችን በማስቀጠል የኢትዮጵያን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሁሉም ጥረት ሊታከልበት ይገባል ብለዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፤ የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ የግብርናው ዘርፍ በእውቀትና በቴክኖሎጂ ከተመራ ስኬታማ መሆን እንደሚቻል ጥሩ ማሳያ ነው ብለዋል።   በክልሉ በተለይም በቡና፣ ሰሊጥ፣ ቅመማቅመም፣ ማርና የእንስሳት ተዋጽኦ ሰፊ ኃብት መኖሩን ጠቅሰው፤ በአግባቡ ማልማት ከተቻለ አገር መለወጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። በሁሉም አካባቢዎች ኢትዮጵያ ኃብቷን ማልማት ከቻለች እድገትና ብልጽግናዋን በአጭር ጊዜ ማሳካት ያስችላልም ነው ያሉት። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በግብርናው መስክ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ለአገር እድገትና ለዜጎች የኑሮ መሻሻል ትልቅ ተስፋ የሰነቀ መሆኑን ገልጸዋል።   በሲዳማ ከክልል ባለፈ ለአገራዊ ኢኮኖሚ እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከት የሚያስችል እምቅ ኃብት በመኖሩ የልማት ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው፤ የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይን እስካሁን ከ50 ሺህ በላይ ሰዎች የጎበኙት መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣዩ እሑድ የሚጠናቀቅ መሆኑን ጠቁመዋል። አውደ-ርዕዩ የግብርናውን ዘርፍ የሚያጠናክር ትልቅ ውጤት የተገኘበት መሆኑን ገልጸው፤ የጎብኝዎችም ፍላጎትና ተነሳሽነት ከተገመተው በላይ መሆኑን ተናግረዋል።   በግብርና ሚኒስቴር፣ በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት እና ኢትዮ-ቴሌኮም በጋራ የተዘጋጀው የግብርና ሳይንስ አውደ-ርዕይ የግብርናው ዘርፍ ያለበትን ደረጃ የሚያሳዩ ምርቶች፣ የግብርና ቴክኖሎጂዎች እና የምርምር ውጤቶች ቀርበውበታል።  
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አገልግሎቱ ለተጠቃሚዎች በድምፅ፣ በምስልና በሌሎችም አማራጮች አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መተግበሪያ ይፋ አደረገ
Jun 1, 2023 42
  አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ለተጠቃሚዎች በድምፅ፣ በምስልና በሌሎችም አማራጮች አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መተግበሪያ ይፋ አደረገ። የተቀናጀ የቤተ-መጻሐፍት የቤተ-መዛግብትና ሪከርድ ማኔጅመንት (ኢላርም) መተግበሪያ በ31 ሚሊዮን ብር ወጪ በአንድ ዓመት የተከናወነ ፕሮጀክት መሆኑም ታውቋል። የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዳይሬክተር ይኩኖ አምላክ መዝገቡ መተግበሪያው (ሶፍትዌሩ) ለፈጣን አገልግሎት ተደራሽነት የላቀ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። የበርካታ መጻሕፍቶችና ሰነዶች ሃብት ባለው ቤተ መጽሃፍት ተጠቃሚዎች የሚፈልጉትን መጻሕፍት፣ በድምፅ፣ በምስልና ሌሎችንም አማራጮች በመተግበሪያው የተቀላጠፈ አገልግሎት የሚያገኙ መሆኑን ገልጸዋል። የአገልግሎቱ የኢንፎርሚሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር ኤልሳቤጥ አሸናፊ፤ የመተግበሪያው እውን መሆን የሪከርድና ማኅደር ክፍል በደንብ ተደራጅቶ አገልግሎት እንዲሰጥም ያግዛል ብለዋል። በዚህም የቤተ-መጻሕፍቱን ካታሎጎች ማንኛውም ሰው ባለበት ስፍራ ሆኖ በሚጠቀምበት ዌብሳይት ፖርታል በመግባት ማግኘት እንደሚችል ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በ1936 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ለቤተመጻሕፍቱ ባበረከቱት መጻሕፍት ሥራ መጀመሩን መረጃዎች ያመለክታሉ።
የስምጥ ሸለቆ ምዕራፍ 3 ግድብ የግንባታ ጥናት የውል ስምምነት ተፈረመ
Jun 1, 2023 54
ሀዋሳ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ)፡- ከ44 እስከለ 50 ሜጋ ዋት በላይ ሀይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል የተባለለት የስምጥ ሸለቆ ምዕራፍ 3 መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት የጥናትና ዲዛይን ስራ የውል ስምምነት ተፈረመ። በኦሮሚያ ክልል በቦረና በደቡብ ክልል ደቡብ የኮንሶ ውሃ አጠር አካባቢወች በሰገን ወንዝ ላይ ተንተርሶ የሚገነባው ግድቡ ሃይል ከማመንጨት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሏል። የፕሮጀክቱ አሰሪ መስሪያ ቤት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጥናቱን ከሚያካሂደው ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽንና ቁጥጥር ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር በሀዋሳ ስምምነት ተፈራርመዋል። በስምምነቱ ላይ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ እንዳሉት ውሃ አጠር በሆነው የቦረናና ኮንሶ አዋሳኝ አከባቢዎች በሚገኝ ተፋሰስ በሰገን ወንዝ ላይ መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመገንባት ዕቅድ ተይዟል። ሀገራችን የኤሌክትሪክ ሃይልን በተለያዩ አማራጮች እያሰፋች ትገኛለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም ለታዳጊ ኢኮኖሚያችን የሃይል አቅርቦት አማራጭ ወሳኝ መሆኑን ከግንዛቤ በማስገባት በትኩረት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል። ግንባታ ለማካሄድ የቅድመ አዋጭነትና አዋጭነት ጥናት ለማካሄድ የውል ስምምነት የተፈረመው የስምጥ ሸለቆ ምዕራፍ 3 መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክት ከ44 እስከ 50 ሜጋ ዋት በላይ ሃይል ለማመንጨት የታሰበ መሆኑን አስረድተዋል። ፕሮጀክቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዲኖረው ተደርጎ እንዲጠና የታሰበ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ ከ26 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በመስኖ የማልማት አቅም ያለው መሆኑን ገልጸዋል።   ፕሮጀክቱን ተከትሎ የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ሎጆችና ሌሎች የመዝናኛ አማራጮችም ኮንሶና አከባቢው ላይ የሚታወቀውን የቱሪዝም ፍሰት ይበልጥ በማስፋት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማጠናከር ይረዳል ተብሎ መታሰቡንም አብራርተዋል። እንደ ሀገር ሃይል ማመንጨትና የአቅርቦት ስራዎች በአብዛኛው በጊቤና አባይ ተፋሰስ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አንስተው በዚህም የተፈጥሮ ሆነ መሰል አደጋዎች ቢከሰት ሊመጣ የሚችለውን ጫና አስቀድሞ ለመከላከል የተፋሰስ አጠቃቀማችንና የሃይል ስብጥር ከፍ ለማድረግ የሚያግዝ ነው ብለዋል። ግንባታው የሚካሄድበት የሰገን ወንዝ ፍሰቱ በሀገር ውስጥ ብቻ በመሆኑ ስራውን ለማከናወን ምቹ አጋጣሚ መሆኑም ተናግረዋል። ከ60 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚካሄደው የቅድመ አዋጭነትና የአዋጭነት ጥናት በሚቀጥሉት 18 ወራት የሚካሄድ ነው የተባለው። ጥናቱ እንደተጠናቀቀም ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና የግል አልሚዎች ተረክበው ወደ ግንባታ እንዲገቡ እንደሚደረግ ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። ግንባታውን የሚያካሂደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽንና ቁጥጥር ስራዎች ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ተሾመ ሲዳላ ግድቡ በሚያርፍበት አከባቢ የሚኖረውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ላይ ጥናት እንደሚደረግ ተናግረዋል። በውሉ መሰረት የባለሙያዎች ስብጥርና ልምድ በመጠቀም የቅድመ አዋጭነትና የአዋጭነት ጥናቱን በ18 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በፊርማው ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የደቡብ ክልል ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ በበኩላቸው በክልሉ የሚነሱ የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሰጠው ዕድል አመስግነዋል። በዛሬው ዕለት የተፈረመው የሃይል ማመንጫ ግንባታ ስራው አካባቢው በስምጥ ሸለቆ ያለና ውሃ አጠር በመሆኑ በተደጋጋሚ የሚከሰትን ድርቅ ከመከላከል አንጻር ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው ነው ያሉት። የጥናት ስራው በተገቢውና በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በክልሉ የሚገኙ ባለሙያዎችና ባለ ድርሻ አካላትን በማቀናጀትና ማህበረሰቡን በማሳተፍ ጠንካራ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል በቦረና በደቡብ ክልል ደቡብ የኮንሶ ውሃ አጠር አካባቢወች በሰገን ወንዝ ላይ ተንተርሶ የሚገነባው ግድቡ ከ44 እስከ 50 ሜጋ ዋት ሃይል ከማመንጨት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሏል። የፕሮጀክቱ አሰሪ መስሪያ ቤት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጥናቱን ከሚያካሂደው ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽንና ቁጥጥር ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር በሀዋሳ ስምምነት ተፈራርመዋል። በስምምነቱ ላይ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ እንዳሉት ውሃ አጠር በሆነው የቦረናና ኮንሶ አዋሳኝ አከባቢዎች በሚገኝ ተፋሰስ በሰገን ወንዝ ላይ መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመገንባት ዕቅድ ተይዟል። ሀገራችን የኤሌክትሪክ ሃይልን በተለያዩ አማራጮች እያሰፋች ትገኛለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም ለታዳጊ ኢኮኖሚያችን የሃይል አቅርቦት አማራጭ ወሳኝ መሆኑን ከግንዛቤ በማስገባት በትኩረት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል። ግንባታ ለማካሄድ የቅድመ አዋጭነትና አዋጭነት ጥናት ለማካሄድ የውል ስምምነት የተፈረመው የስምጥ ሸለቆ ምዕራፍ 3 መካከለኛ የሃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክት ከ44 እስከ 50 ሜጋ ዋት በላይ ሃይል ለማመንጨት የታሰበ መሆኑን አስረድተዋል። ፕሮጀክቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዲኖረው ተደርጎ እንዲጠና የታሰበ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ ከ26 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በመስኖ የማልማት አቅም ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱን ተከትሎ የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ሎጆችና ሌሎች የመዝናኛ አማራጮችም ኮንሶና አከባቢው ላይ የሚታወቀውን የቱሪዝም ፍሰት ይበልጥ በማስፋት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማጠናከር ይረዳል ተብሎ መታሰቡንም አብራርተዋል። እንደ ሀገር ሃይል ማመንጨትና የአቅርቦት ስራዎች በአብዛኛው በጊቤና አባይ ተፋሰስ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አንስተው በዚህም የተፈጥሮ ሆነ መሰል አደጋዎች ቢከሰት ሊመጣ የሚችለውን ጫና አስቀድሞ ለመከላከል የተፋሰስ አጠቃቀማችንና የሃይል ስብጥር ከፍ ለማድረግ የሚያግዝ ነው ብለዋል። ግንባታው የሚካሄድበት የሰገን ወንዝ ፍሰቱ በሀገር ውስጥ ብቻ በመሆኑ ስራውን ለማከናወን ምቹ አጋጣሚ መሆኑም ተናግረዋል። ከ60 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚካሄደው የቅድመ አዋጭነትና የአዋጭነት ጥናት በሚቀጥሉት 18 ወራት የሚካሄድ ነው የተባለው። ጥናቱ እንደተጠናቀቀም ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና የግል አልሚዎች ተረክበው ወደ ግንባታ እንዲገቡ እንደሚደረግ ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። ግንባታውን የሚያካሂደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽንና ቁጥጥር ስራዎች ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ተሾመ ሲዳላ ግድቡ በሚያርፍበት አከባቢ የሚኖረውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ላይ ጥናት እንደሚደረግ ተናግረዋል።   በውሉ መሰረት የባለሙያዎች ስብጥርና ልምድ በመጠቀም የቅድመ አዋጭነትና የአዋጭነት ጥናቱን በ18 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በፊርማው ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የደቡብ ክልል ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ በበኩላቸው በክልሉ የሚነሱ የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሰጠው ዕድል አመስግነዋል። በዛሬው ዕለት የተፈረመው የሃይል ማመንጫ ግንባታ ስራው አካባቢው በስምጥ ሸለቆ ያለና ውሃ አጠር በመሆኑ በተደጋጋሚ የሚከሰትን ድርቅ ከመከላከል አንጻር ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው ነው ያሉት። የጥናት ስራው በተገቢውና በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በክልሉ የሚገኙ ባለሙያዎችና ባለ ድርሻ አካላትን በማቀናጀትና ማህበረሰቡን በማሳተፍ ጠንካራ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
አገራት በሳይበር ምህዳሩ ዘላቂ የሆነ ጥቅም ለማግኘት ትውልድ ተሻጋሪ የአቅም ግንባታ ስራ መስራት ይገባቸዋል - አቶ ሰለሞን ሶካ
Jun 1, 2023 73
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፦ አገራት በሳይበር ምህዳሩ ዘላቂ የሆነ ጥቅም ለማግኘት ትውልድ ተሻጋሪ የአቅም ግንባታ ስራ መስራት እንደሚገባቸው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። በሞሮኮ እየተካሄደ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ጂአይቴክስ) ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን የያዘ ሲሆን "የሳይበር ደህንነት አቅም ግንባታ ስራ ለሙያዊ ልህቀትና ለኢኮኖሚ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት ተደርጓል። በአውደ ርዕዩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በትውልድ መካከል የሚፈጠሩ የእውቀት ክፍተቶችን ለመሙላት ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል። እንደ ኢመደአ ያሉ የሳይበር ምህዳር ላይ የተሰማሩ ተቋማት የሰው ኃይል አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ድጋፍ መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢመደአ ብቁ እና ወሳኔ ሰጪ አመራር ለማፍራት የሚያስችሉ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል። የሰው ኃይልን ከትምህርት የተመረቁ ብቻ ይዞ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና ቀጣይነት ያለውን የበቃ የሰው ሃይል ልማት ማስቀጠል ስለማይቻል ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች መልምሎ እና እውቀታቸውን ለማጎልበት መስራት እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት። በተያያዘም የሳይበር ጥቃት ከዓለማችን ቀዳሚ ስጋቶች አንዱ መሆኑንና ምህዳሩ ፍጹም ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች እንደሆነ ተናግረዋል። ከዚህ አንጻር አገራት በሳይበር ምህዳሩ ላይ በሚሰሩ ስራዎች ላይ በትብብርና በቅንጅት ሊሰሩበት እንደሚገባ መግለጻቸውን ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ ነገ ይጠናቀቃል።          
'ጂ አይ ቴክስ አፍሪካ' በሞሮኮ ማራካሽ ከተማ መካሄድ ጀመረ
Jun 1, 2023 92
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- 'ጂ አይ ቴክስ አፍሪካ' 2023 /GITEX Africa 2023/ በሞሮኮ ማራካሽ ከተማ መካሔድ ጀምሯል። በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው 'ጂ አይ ቴክስ አፍሪካ' ላይ ኢትዮጵያ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶክተር) በሚመሩትና የሚኒስቴሩ የስራ ኃላፊዎችና በውድድር የተመረጡ የቴክኖሎጂ ጀማሪ ካምፓኒዎች (ስታርታፖች) በተካተቱበት የልዑካን ቡድን እየተሳተፈች ትገኛለች። በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከናወነ የሚገኘው 'ጂ አይ ቴክስ አፍሪካ' ተቀዳሚ ዓላማ በአህጉሯ እየተካሄደ የሚገኘውን የቴክኖሎጂ አብዮት ለተቀረው ዓለም ማስተዋወቅ ነው። ባለፋት ሁለት አመታት መሠረታቸውን አፍሪካ ያደረጉ በርካታ ጀማሪ የቴክኖሎጂ ፈጣሪ ካምፓኒዎች በዓለምአቀፉ መድረክ በስፋት መታየት እና ተጽዕኖ መፍጠር ጀምረዋል። ዶክተር በለጠ ኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞን እውን ለማድረግ ባለፉት ሶስት ዓመታት ያከናወነቻቸውን ተግባራት፣ እያደረገች ያለውን ጥረቶች፣ የተገኙ ውጤቶችን እና ያጋጠሙ ችግሮችን ማብራሪያ መስጠታቸውን ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ሚኒስትሩ በቀጣይ እንደ አፍሪካ በቅንጅት መካሄድ አለባቸው ባሏቸው ጉዳዮች ላይም ሃሳባቸውን ለመድረኩ አጋርተዋል። አክለውም ኢትዮጵያ በርካታ ለስራ ዝግጁ የሆኑ ወጣቶች፣ ቴክኖሎጂን ትኩረት ያደረጉ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የዲጂታል ዘርፍ ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ የህግ ማዕቀፍና ለስራ ዝግጁ የሆነ የአይ ሲቲ ፓርክ እንዳላትም አሳውቀዋል። ሚኒስትሩ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስ ተጠቃሚ እንዲሆኑና እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል ።          
ስፖርት
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ዛሬ ይጀመራል 
Jun 1, 2023 74
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ሁለት ጨዋታዎች በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋሉ። በመርሃ ግብሩ ሲዳማ ቡና ከአርባ ምንጭ ከተማ ከቀኑ 7 ሰአት ላይ ይጫወታሉ። በደረጃ ሰንጠረዡ ሲዳማ ቡና በ34 ነጥብ 10ኛ ደረጃን የያዘ ሲሆን አርባ ምንጭ ከተማ በ29 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሲዳማ ቡና በሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች አራቱን ሲያሸንፍ በአንዱ አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው አርባ ምንጭ ከተማ በአንጻሩ ባለፉት አምስት ጨዋታዎች አንድ ጊዜ ሲያሸንፍ በአራቱ ነጥብ ተጋርቷል። ጨዋታው ሲዳማ ቡና ከወራጅ ቀጠና ስጋት ለመራቅ እንዲሁም አርባ ምንጭ ከተማ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት የሚያደርጉት ጨዋታ መሆኑ ተጠባቂ ያደርገዋል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያ ዙር ያደረጉት ጨዋታ ሶስት እኩል በሆነ ውጤት መጠናቀቁ ይታወሳል። በሌላኛው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ -ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከለገጣፎ ለገዳዲ ከቀኑ 10 ሰአት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በደረጃ ሰንጠረዡ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ55 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ የተቀመጠ ሲሆን ከፕሪሚየር ሊጉ መውረዱን ያረጋገጠው ለገጣፎ ለገዳዲ በ15 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ቅዱስ ጊዮርጊስ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሶስቱ አሸንፎ በአንዱ ተሸንፎ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው ለገጣፎ ለገዳዲ ባለፉት አምስት ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ሲሆን በሶስቱ ተሸንፏል በአንዱ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ካሸነፈ ከተከታዩ ባህር ዳር ከተማ ጋር ያለውን ልዩነት ወደ ስምንት ከፍ ያደርጋል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ 4 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር እስከ ግንቦት 27/ 2015 ይቆያል። የፕሪሚየር ሊጉ የውድድር እና ስነ ስርዓት ኮሚቴ በሃዋሳ ከተማ አመሻሽ ላይ በሚጥለው ከባድ ዝናብ ምክንያት የ27ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ላይ የሰዓት ማስተካከያ በማድረግ በ9 ሰዓት እንዲጀምሩ ፕሮግራም የወጣላቸው ጨዋታዎች በሙሉ 7 ሰዓት እንዲሁም በ12 ሰዓት ይጀምሩ የነበሩ ጨዋታዎች ደግሞ 10 ሰዓት ላይ እንዲጀመሩ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል። በተጨማሪም ተጀምሮ በዝናብ ምክንያት የተቋረጠ ጨዋታ ካለ በማግስቱ ከጠዋቱ 4 ሰዓት ጀምሮ በሃዋሳ አርተፊሻል ሜዳ ላይ እንደሚጠናቀቅም ገልጿል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ከጎፈሬ የስፖርት ትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር ስምምነት ተፈራረመ
May 31, 2023 73
አዲስ አበባ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ሀገር በቀል የስፖርት ትጥቅ አምራች ከሆነው ጎፈሬ ድርጅቱ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ በስምምነቱ መሰረት ኩባንያው በሁሉም እድሜ እርከን ለሚመረጡ የብሄራዊ ቡድን ተጫዋቾች የስፖርት ትጥቅ ያቀርባል።   የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን ስምምነቱ ለአራት ወራት የሚቆይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ትጥቁ ለገበያ ከሚቀርብበት ዋጋ 50 በመቶ ቅናሽ እንደሚያገኝ አስታውቀዋል። የጎፈሬ የስፖርት ትጥቅ አምራች ድርጅት ባለቤት አቶ ሳሙኤል መኮንን ኩባንያቸው ከዚህ በፊት ከ17 ዓመት በታች ለሆኑ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እና ለዋናው ብሄራዊ ቡድኑ የስፖርት ትጥቅ ሲያቀርብ እንደነበረ አስታውሰዋል። ይህን ተከትሎ አሁን ላይ ለዋናው ብሄራዊ ቡድን የስፖርት ትጥቅ ለማቅረብ ስምምነት በማድረጋቸው ኩራት እንደተሰማቸው ገልጸዋል ። በስምምነቱ መሰረት ኩባንያው በአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ውድድር ተሳትፎ እያደረገ ለሚገኘው ዋናው ብሄራዊ ትጥቅ ያቀርባል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ብሄራዊ ቡድኑ በመጪው ሰኔ ወደ አሜሪካ በማቅናት ለሚያደርገው የወዳጅነት ጨዋታ የጎፈሬ ምርቶችን እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል ። ጎፈሬ የምርቱን ጥራት በማሻሻል አሁን ላይ ከሀገር ውስጥ ባለፈ ከተለያዩ የውጭ ክለቦች ጋር ስምምነት በማድረግ የስፖርት ትጥቅ እያቀረበ እንደሆነ ገልጸዋል ። በስምምነቱ መሰረት ኩባንያው ለብሄራዊ ቡድኑ ጨዋታና የመለማመጃ የስፖርት ትጥቆችን ያቀርባል ።    
አካባቢ ጥበቃ
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ከ109 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ተዘጋጅተዋል - የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ
Jun 1, 2023 44
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን ለአምስተኛው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ109 ሚሊየን በላይ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ። የመምሪያው ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ለኢዜአ እንዳሉት ለግብርና ምርታማነት በተሰጠው ትኩረት በበጋ መስኖ ስንዴና በመደበኛ የመኸር ሰብል ልማት ውጤታማ የምርት አሰባሰብ ስራ እየተከናወነ ይገኛል። በመደበኛ መስኖ ልማት ስራም ከ52 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በማከናወን 13 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ሰብል ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ14 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል። በመደበኛ የመስኖ ልማት የተቀመጠውን ግብ ከዕቅድ በላይ በማሳካት እንደ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮት፣ ሽንኩርት ሌሎች የአትክልትና ፍራፍሬ ዓይነቶችን ማልማት መቻሉንና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዞኑ የምርታማነት ልማት ስራ እየተሻሻለ መምጣቱን አመልክተዋል። በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ወራትም ከ2 ሺህ ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት የበጋ መስኖ ስንዴን በማልማት እስካሁን ከ80 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ እንደተቻለ ጠቁመዋል። ለአምስተኛው የአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ-ግብር ቅድመ ዝግጅትም እንደዞን ከ109 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኝ መዘጋጀታቸውንና ከዚህም ውስጥ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ የፍራፍሬ ችግኞች እንደሚገኝበት ነው አቶ አበራ ያስረዱት። የፍራፍሬ እጽዋቶችን ማልማት የአርሶ አደሩን የምግብ ፍጆታ በማረጋገጥ የገበያ አማራጭ መፍጠር እንደሚያስችል አመልክተዋል። ለመርሐ-ግብሩ ከ18 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኝ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በአገር አቀፍ ደረጃ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተያዘው አምስተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞች መዘጋጀታቸውን በመጠቆም፤ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞችን በብዛት እንደሚተከሉ ማሳወቃቸው የሚታወስ ነው።
በሲዳማ ክልል በአምስተኛው ዙር አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ94 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል
Jun 1, 2023 44
ሀዋሳ፣ ግንቦት 24 ቀን 2015 (ኢዜአ) በሲዳማ ክልል በአምስተኛው ዙር አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ከ94 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸውን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ገለጸ። የችግኞቹን መጠነ ጽድቀት ከፍ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎችም ከወዲሁ እየተሰሩ እንደሆነ ተጠቁሟል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ፍቅረኢየሱስ አሸናፊ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በክልሉ በዘንድሮ መርሃ ግብር 316 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል ታቅዷል። ከሚያዚያ ወር ወዲህ አርሶ አደሮችን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ በተካሄደ ንቅናቄ የእቅዱን 30 በመቶ መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል። አብዛኛዎቹ የተተከሉት ችግኞች የአየር ንብረት ለውጥ ተፅእኖን ለመቋቋም አስተዋጽኦ ያላቸው እንደሆነ ጠቅሰው፤ እንደ ዋንዛ፣ ግራር፣ ጽድ፣ ቢርቢራ የመሳሰሉ ሀገር በቀል እና ለአርሶ አደሩ በቋሚነት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የቡናና የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸውን ተናግረዋል። በክልሉ ለችግኝ ተከላ የሚሆኑ ከ200 በላይ ተራራዎች፣ የተራቆቱ አካባቢዎችና ሌሎችም መትከያ ስፍራዎች ተለይተው ከክልል ጀምሮ ባሉ ሁሉም መዋቅሮች ንቅናቄ በመፍጠር ዕቅዱን ለማሳካት እየተሰራ እንደሆነ አመልክተዋል። ለተተከሉት ችግኞች እንክብካቤ በማድረግ እንዲጸድቁ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። እንደ ምክትል ቢሮ ኃላፊው ገለፃ፤ በክልሉ ባለፉት አራት ዓመታት አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከ850 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መትከል ተችሏል። ይህም ለአፈርና ውሃ እቀባ እንዲሁም የመሬትን ለምነትና እርጥበትን በማሻሻል ለምርትና ምርታማነት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አስረድተዋል። ከተተከሉት ፍራፍሬዎች መካከል የተሻሻሉ የአቮካዶ ዝርያዎች ምርት በመስጠት ለይርጋለም የተቀናጀ ግብርና ፓርክ ግብዓት ሆኖ እየቀረበ እንደሆነም ተናግረዋል። የዳራ ሆጢልቾ ወረዳ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መንግስቱ ማቲዎስ በበኩላቸው ለዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ስኬታማነት በትኩረት እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል። ወረዳው ዘንድሮ 5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል ማቀዱን ጠቅሰው፤ እስካሁን 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ችግኝ መትከል መቻሉን አመልክተዋል። ቀሪውን ችግኝ ለመትከል በህብረተሰብ ተሳትፎ የችግኝ ጉድጓድ ቁፋሮ በዘመቻ እየተካሄደ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በችግኝ ተከላ ተራቁቶ የነበረ ከ736 ሄክታር በላይ መሬት መልሶ በማገገም ወደ ልማት መግባቱን ጠቅሰው፤ በወረዳው የችግኝ መጠነ ጽድቀት 92 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል። እየተከናወነ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለመሬት እርጥበትና ለምነት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ያሉት ደግሞ የብላቴ ዙሪያ ወረዳ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ላሚሶ ዴራሞ ናቸው። ልማትን በተቀናጀ መንገድ መምራት የሚያስችል ንቅናቄ ተፈጥሮ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ዘንድሮ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ችግኝ በወረዳው ይተከላል ብለዋል።  
በጅማና ምስራቅ ወለጋ ዞኖች ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ቅድመ ዝግጀት ስራ እየተጠናቀቀ መሆኑ ተገለጸ
Jun 1, 2023 52
ጅማ/ነቀምት ግንቦት 24/2015:-በጅማና ምስራቅ ወለጋ ዞኖች ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ቅድመ ዝግጀት እየተጠናቀቀ መሆኑን የየዞኖቹ ግብርና ጽህፈት ቤቶች ገለጹ። በጅማ ዞን ብቻ ለ5ኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ከ350 ሚሊዮን በላይ ችግኞች የሚተከሉ መሆኑ ተገለጿል። የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ መሀመድ ጣሃ አባፊጣ እንደተናገሩት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በዘመቻ እንዲሁም በተቋማት አማካይነት የሚከወን መሆኑንና የመትከያ ቦታዎች እየተዘጋጁ ስለመሆኑ ገልጸዋል።   በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከዚህ ቀደም በዞኑ ያልተለመዱ እንደ ቀርቃሃ እና ቴምር ያሉ ችግኞችም የሚተከሉ ይሆናል ብለዋል። ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞችን ከመንከባከብ አንጻር የጽድቀት መጠኑ 80 በመቶ ሲሆን ይህም የሚበረታታ መሆኑን ነው ሀላፊው የተናገሩት። በዞኑ የነዲ ጊቤ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ነዚፋ አወል፣ በዚህኛው ዙር 100 ችግኝ ለመትከል ቦታ ያዘጋጁ መሆኑን እና በዘመቻ የሚተከለውንም ለመሳተፍ ተዘጋጅተዋል። ሌላው የዴዶ ወረዳ አርሶ አደር ወጣት ናስር አባ ጀበል በበኩሉ በየአመቱ የተለያዩ ችግኞችን በማሳው ዳርቻ እንደሚተክል ገልጾ ዘንድሮም 50 የተመረጡ የዛፍ ችግኞችን ለመትከል መዘጋጀቱን ተናግሯል። ''ከዚህ በፊት የተከልኳቸውን ችግኞች በመንከባከብ ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሰዋል'' ያለው ወጣቱ ''አሁንም እንደ ዋንዛ እና ግራር የመሳሰሉ ዞፎችን እተክላለሁ'' ብሏል። በተመሳሳይ በምሰራቅ ወለጋ ዞን በመጪው ክረምት 400 ሚሊዮን ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገልጿል፡፡ በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ሀብት ስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ደሳለኝ በለታ በዞኑ በተለያዩ ወረዳዎች የችግኝ እና ጉድጓድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። እሰካሁን በተሰራ ስራ በ2 ሺህ 148 ችግኝ ጣቢያዎች 378 ሚልዮን ችግኝ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። እየተዘጋጁ ከሚገኙት ችግኞች መካከል ለእንስሳት መኖ፣ ቀርከሃ፣ ፍራፍሬ እና የተለያዩ ዛፎች ይገኙበታል ብለዋል፡፡ በዞኑ ለዚሁ አላማ የሚውል 39 ሺህ ሔክታር መሬት ተዘጋጀ ሲሆን 182 ሚልዮን የችግኝ መትከያ ጉድጓድ መዘጋጀቱን ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሌሎች የአፍሪካ አገራት አርአያ የሚሆን ነው - ኢሲኤ 
Jun 1, 2023 87
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሌሎች የአፍሪካ አገራት ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ የአየር ንብረት ለውጥና የተፈጥሮ ሃብት ዳይሬክተር ዦን ፖል አደም ተናገሩ። ዳይሬክተሩ ዦን ፖል አደም ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የምታካሂደው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የብዝሃ ሕይወት ጥበቃን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው። ያም ብቻ ሳይሆን በመርሃ ግብሩ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥና የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራት ማቀፉንም ነው የጠቆሙት። ለአብነትም ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ለመፍጠር የሚያስችሉ ቡናን ማልማትና ሌሎችም ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያላቸው እንቅስቃሴዎች እንዳሉት ተናግረዋል። ጎን ለጎንም ኢትዮጵያ በተፋሰስ አካባቢ ብዝሃ ሕይወት በመንከባከብ የውሃ ሃብትን ለመንከባከብ እየሰራች ያለው ሥራ የሚደነቅ መሆኑንም አንስተዋል። በመሆኑም ይህ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው የአረንጓዴ አሻራ ለሌሎች የአፍሪካ አገራት በአርአያነት የሚጠቀስ መርኃ ግብር መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። ተቋማቸውም ይህንን የኢትዮጵያ ጥረት ስኬታማ ለማድረግ የሙያ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ አገራት ኢኮኖሚያዊ ለውጥን እውን ለማድረግ የብዝሃ ሕይወት ጥበቃ ዋነኛው መሆኑን ገልጸው በዘርፉ ሕዝቡን በበቂ ሁኔታ ተጠቃሚ ሳይሆን መቆየቱን ጠቁመዋል። በመሆኑም የአፍሪካ አገራት ለዘርፉ አስፈላጊውን ትኩረትና በመስጠትና ከዘርፉ የሚያገኙትን ጥቅም ከፍ በማድረግ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት። የአፍሪካ አገራት በግብርናው ዘርፍ ዘላቂነት ያለው የእሴት ሰንሰለት በመፍጠር በቱሪዝም ዘርፍ ገቢን ማሳደግ እንደሚገባ ዳይሬክተር ዦን ፖል አደም ተናግረዋል።      
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ፕሬዝዳንት ፑቲን ለአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
May 25, 2023 209
አዲስ አበባ ግንቦት 17/2015 (ኢዜአ)፦የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን ለቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለአሁኑ የአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንከዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት ለአፍሪካውያን የድል ምልክት ነው ያሉ ሲሆን የአፍሪካውያን የነጻነት፣የሰላምና የብልጽግና ፍላጎት ማሳያ ነው ብለዋል። ህብረቱ ከተመሰረተበት ግዜ አንስቶ ለብዙ አስርተ ዓመታት በዓለም አቀፍ መድረኮች አፍሪካውያንን በመወከል የባለብዙ ወገን ውይይቶችንና ትብብርን በማጎልበት ትልቅ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት ለችግሮቻቸው በጋራ ምላሽ የሚሰጡበትን መንግድ ያመቻቸ መሆኑን ጠቁመው አህጉራዊ ትብብርን በተለያዩ መስኮች እንዲያጠናከሩም መንገድ ከፍቷል ብለዋል። በዚህም ለአፍሪካ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት የላቀ ሚና ማበርከቱንና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ያላትን ተሳትፎ እንድታሳድግ ህብረቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ሩሲያ ከአፍሪካ አጋሮቿ ጋር ያላትን ወዳጅነት ለማጠናከር ልዩ ትኩረት ትሰጣለች ያሉት ፕሬዝዳንቱ እ.አ.አ በ2019 የተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ -ሩሲያ ጉባኤ በአፍሪካና በሩሲያ መካከል ያሉ ትብብሮች እንዲጠናከሩ አስችሏል ብለዋል። በመጪው ሃምሌ ወር በሩሲያ የሚካሄደው ሁለተኛ የአፍሪካ ሩሲያ ጉባኤም ሩሲያ ከአፍሪካ ጋር ለሚኖራት ትብብር አዲስ ምዕራፍ እንደሚፈጥር ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 3575
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተገለጸ
Dec 20, 2022 1646
አዲስ አበባ ታኅሳስ 11/2015 (ኢዜአ) አህጉራዊው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና አፍሪካ ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ግንኙነትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተመላከተ። የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ከአፍሪካ ጋር ያላት የንግድ ትስስር ከባህረ-ሰላጤው ሃገራት መካከል በቀዳሚነት እንደሚጠቀስም ተገልጿል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዊሊያም ስቴንሀውስ ከሲ ጂ ቲ ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በተለይም ዱባይ የአፍሪካን ንግድና ኢንቨስትመንት በተመለከተ ዋና ማዕከል ሆናለች ብለዋል። በዱባይ 25ሺህ ገደማ የአፍሪካ ካምፓኒዎች እንደሚንቀሳቀሱ አመልክተው ይህም ሀገሪቱ በነጻ የንግድ ቀጣናው የቢዝነስ አጋር እንድትሆን አስችሏታል ነው ያሉት። አፍሪካውያን ባለሃብቶች የግብይት ማዕከላቸውን በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በማድረግና ምርቶችን ወደ አህጉሪቷ በማስገባት በነጻ ንግድ ቀጣናው ስር የገልፍ ሀገራትን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደጉት እንደሚገኝም አስገንዝበዋል። የዱባይ ወደብ በአፍሪካ ያለው ተደራሽነት መስፋፋትም አፍሪካ ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ጋር የሚኖራትን የሎጀስቲክስ አቅርቦት እንደሚያሳድግ በመረጃው ተመላክቷል። ከገልፍ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት ከኢኮኖሚያዊ ትስስር ባለፈ ዲፕሎማሲያዊና ወንድማማችነትን መሠረት ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤሜሬት የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ ናቸው። አምባሳደሩ እንደሚሉት ከመካከለኛው ምስራቅ መነሻቸውን ያደረጉ ባለሃብቶችና የቢዝነስ ሰዎች ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጋር በልዩ ልዩ ዘርፎች ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ይገኛል። እ.አ.አ በጥር 2021 ተግባራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ከአጀንዳ 2063 ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የአህጉሪቱን ወሳኝ የኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም የዲጂታል ንግድ፣ የኢንቨስትመንት ትስስርና ሌሎች የንግድ ግንኙነቶችን በነጻ የንግድ ቀጣና ለማከናውን የተካሄደ ስምምነት ነው።
ሐተታዎች
አፋጣኝ መፍትሔ የሚያሻው የምርታማነት ፀር
May 27, 2023 130
  (ኤልያስ ጅብሪል) አሲዳማ አፈር የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከሰባት በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al+3) ንጥረ- ነገሮች የሚበዙበት አፈር ማለት ነው፡፡ የአፈር አሲዳማነት በሀገራችን በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ የሚገኝ የአፈር ለምነት ችግር ሲሆን፤ ከፍተኛ ዝናብ የሚያገኙና በምርታማነታቸው የተሻሉ ናቸው የሚባሉትን የሀገሪቱን አካባቢዎች ጭምር እየጎዳ መሆኑንም ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት፡፡ የአፈር ጤንነት ችግሮች በሦስት ዋና ዋና መንገዶች ይገለፃሉ፡፡ ይኸውም አሲዳማነት፣ የጨዋማነት ችግር የሚነሳበትና ኮትቻማ/ጥቁር ወይም መረሬ አፈር/ ብሎ ማስቀመጥ እንደሚቻል በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊ ፋኖሴ መኮንን ይናገራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ከ15 ሚሊየን ሄክታር በላይ የሚታረስ መሬት ሲኖር ወደ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በአሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነ ነው የጠቀሱት፡፡ አፈር ሰብሎች የሚፈልጓቸውን ንጥረ-ነገሮች በተሟላና በተመጣጠነ መልኩ ሳይዝ ሲቀር ምርታማነት ጥያቄ ውስጥ እንደሚወድቅ አቶ ፋኖሴ ይገልጻሉ። ከዚህ አኳያ በኢትዮጵያ ከ1 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጎዳ በመሆኑ ምርታማነቱ ምንም በሚባል ደረጃ የሚቀመጥ መሆኑን ይጠቁማሉ። እፅዋት ከአየር፣ ውሃና የፀሐይ ብርሃን በተጨማሪ 18 ዓይነት ንጥረ-ነገሮችን ከአፈር ውስጥ ሊያገኙ እንደሚችሉ ነው ኃላፊው የገለጹት፡፡ የአፈር አሲዳማነት መንስኤዎች አሲዳማነት በአንድ ጊዜ ተፈጥሮ የሚቆይ ሳይሆን በሂደት እየጨመረ እና እየተስፋፋ የሚሄድ ክስተት ነው፡፡ ለአፈር አሲዳማነት በዋነኝነት የዝናብ መብዛት፣ የአፈር መሸርሸር፣ የሰብል ተረፈ-ምርት ሙሉ በሙሉ ከማሳ ማንሳት እና ፍግ አለመጠቀም፣ እንዲሁም አሲዳማ ዝናብ የመሳሰሉት አፈር ውስጥ ያሉ ለተክሉ እድገት ጠቃሚ ንጥረ-ነገሮች እንዲሟጠጡ እንደሚያደርግ በመንስኤነት ይጠቀሳሉ። የአፈር አሲዳማነት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚስተዋል ሲሆን ለአብነትም አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ተጠቃሾች እንደሆኑ አቶ ፋኖሴ ተናግረዋል፡፡ አሲዳማ አፈርን በኖራ የማከም ዘዴ አሲዳማ አፈርን ለመከላከል በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ መንገዶች ከሚወሰዱ እርምጃዎች ባሻገር አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ በዋናነት የሚጠቀስ መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ አፅንዖት ሰጥተው የተናገሩት፡፡ የተለያዩ አፈርን የማከሚያ ግብአቶች ያሉ ቢሆንም በቀላሉ ከመገኘትና ከዋጋው ርካሽነት አንፃር ካልሽየም ካርቦኔት ወይም “ የግብርና ኖራ" እየተባለ የሚጠራው በስፋት አገልግሎት ላይ እንደሚውል ገልጸዋል፡፡ ወደ 15 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር የሚታረስ መሬት ሲኖር፤ ከዚህ ውስጥ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር ወይም ከ43 በመቶ የማያንሰው በአሲዳማ አፈር የተጠቃ መሆኑን ጠቅሰው፤ ወደ 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነው በጠንካራ አሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነና በኖራ መታከም ያለበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ጠንካራ አሲዳማ አፈር ስንል የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከ 5 ነጥብ 5 በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al3+) ካታየኖች የሚበዙበት አፈር ሲሆን፤ የእነዚህ ካታየኖች መብዛት የሰብሎችን ሥር በመመረዝ በዕድገታቸው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን እንደሚፈጥር ነው ከግብርና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ የሚጠቁመው፡፡ ፒ ኤች መጠኑ ከሰባት ወደ ዜሮ እየቀነሰ ሲሄድ የአሲድነቱ ጥንካሬ የሚጨምር ሲሆን ከሰባት ወደ 14 ሲጨምር የጨዋማነቱ ባህሪ እንደሚጨምር ነው የዘርፉ ባለሙያዎች የሚያስቀምጡት። በአገራችን ሁኔታ አሲዳማ አፈርን ለማከም ኖራ መጠቀም የሚያስፈልገው የአፈሩ ፒ ኤች መጠን ከ5 ነጥብ 5 በታች ሲሆን ነዉ፡፡ ኖራ በተፈጥሮ የሚገኝ የካልሲየም እና የማግኒዚየም ካርቦኔት ሃይድሮኦክሳይድ ውህድ ሲሆን፤ አሲዳማ አፈር ውስጥ በሚጨመርበት ወቅት አሲዳማ አፈር ውስጥ የሚገኙትን አልሙኒየም እና ሃይድሮጂን አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን በመግታት የአፈሩን ፒ ኤች መጠን ከፍ በማድረግ ለእፅዋት እድገት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ በአማካይ በአፈር አሲዳማነት የተጎዳ መሬትን ለማከም በሄክታር 30 ኩንታል የግብርና ኖራ እንደሚያስፈልግ ባለሙያዎች ይመክራሉ። በአሲዳማነት የተጠቃ መሬት አሲዳማነትን የሚቋቋሙ ሰብሎች ካልተዘሩበት ወይም አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ ካልተሰራ የሚሰጠውን የአፈር ማዳበሪያ ከጥቅም ውጭ በማድረግ ለኪሳራ ይዳርገናል ነው ያሉት፡፡ እንደ አኩሪ አተር፣ ካሳቫ፣ አናናስ፣ ዳጉሳ፣ ቡና፣ ሻይ እንዲሁም የስንዴ ዝርያዎች አሲድን የመቋቋም ባህሪ እንዳላቸውም ተመላክቷል፡፡ ግብርና ሚኒስቴር በአሲዳማነት ከተጠቃው 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነውን በአሥር ዓመት ውስጥ ለማከም ዕቅድ የያዘ ቢሆንም በዕቅዱ መሰረት በዓመት 400 ሺህ ሄክታር መሬት ለማከም ወደ 5 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት፡፡ ከበጀት አንጻር ይህን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በየዓመቱ ከመንግሥት ካዝና ማግኘት ከባድ በመሆኑ ከእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች፣ ከአጋር አካላት ድጋፍ ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን ነው ያስታወቁት። ምንም እንኳን በአሲዳማነት የተጠቃውን አፈር ማከም ወጪው ከፍተኛ ቢሆንም አፈሩ ሳይታከም በቆየ ቁጥር ከምርት ውጭ የመሆን ዕድሉ እየጨመረ ስለሚሄድ አገርን የሚያሳጣው ዋጋ ከፍተኛ እንደሚሆን በውል መረዳት ያሻል። በዚህም የአፈር አሲዳማነት ጉዳይ መፍትሔ ካልተሰጠው ምርታማነትን ከ50 በመቶ እስከ 100 በመቶ ሊያሳጣ እንደሚችል ነው በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊው ፋኖሴ መኮንን የሚናገሩት፡፡ ከአፈር አሲዳማነት የተነሳ በየዓመቱ ወደ 9 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በኢትዮጵያ ደረጃ በስንዴ ከሚሸፈነው መሬት ብቻ እየታጣ እንደሆነ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ይህ በስንዴ ብቻ ከሚሸፈን መሬት የተወሰደ ግምት ሲሆን በገብስ፣ ጤፍ ወዘተ… ቢታሰብ ምን ያህል የምርት ማሽቆልቆል እንደሚያስከትል ማወቅ ይቻላል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ የስንዴ ምርት በአማካይ በሄክታር እስከ 40 ኩንታል ምርት ሊሰጥ ይችላል፤ ሆኖም ግን የአፈር ጤንነቱን በመጠበቅ አስፈላጊውን ግብአት የምንጠቀም ከሆነ በሄክታር 60 ኩንታል በማምረት አገራችን የጀመረችውን ምርትና ምርታማነትን የማረጋገጥ ሥራ ማከናወን ያስችለናል ነው ያሉት፡፡ ይህንንም ከግብ ለማድረስ የግብርና ሚኒስቴር የመጀመሪያው የትኩረት አቅጣጫው የአሲዳማ አፈር ልማት መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ ያስረዱት፡፡ አሲዳማ አፈሩን ለመከላከል በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ባለፉት ሦስት ዓመታት 38ሺህ 369 ሄክታር መሬት በኖራ የማከም ሥራ መከናወኑ ተገልጿል። ይህ ከሚኒስቴሩ ዕቅድ አኳያ ሲታይ በጣም ዝቅተኛ አፈጻጸም ነው። የአፈር አሲዳማነትን ለማከም የግብርና ኖራ ምርት ላይ የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች አቅርቦቱን በሚፈለገው ደረጃ ቢያቀርቡም፤ የኖራ ምርቱ በብዛት ያለበት ቦታ እና አሲዳማ መሬቱ የሚገኝበት ርቀት በተቃራኒው በመሆኑ ከትራንስፖርት አንጻር ያለው ችግር ሥራውን አድካሚ እንዳደረገው ነው የሚኒስቴሩ መረጃ የሚያመለክተው። ነገር ግን አርሶ አደሩ አንድ ጊዜ መሬቱን በኖራ ማከም ከቻለ እስከ አምስት ዓመት ሊያገለግለው ይችላል። ከዚያም በኃላ ቢሆን የተወሰነ የምርት መቀነስ እንጂ በምርታማነት ላይ የጎላ ችግር አይኖረውም ነው ያሉት። ስለሆነም ኖራን የመጠቀም ሁኔታ አቅም ያለው አርሶ አደር በግዥ መልክ እንዲጠቀም፤ አቅም የሌለው ደግሞ መንግሥት ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል። እንደ ምዕራብ ኦሮሚያ ነጁ፣ መንዲ፣ ምዕራብ ወለጋ እንዲሁም በአማራ ክልል አዊ ዞን፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አብዛኛውን ወረዳዎች በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጠቁ በመሆናቸው ምርት ለመስጠት የማይችሉበት ደረጃ ላይ እየደረሱ መሆኑን አቶ ፋኖሴ ገልጸዋል። ዝዋይ፣ ሐዋሳ፣ መራቤቴ፣ ደጀን፣ ጉደርና የመሳሰሉት በመንግሥትም ሆነ በግል የግብርና ኖራ ምርት የሚቀርብባቸው ቦታዎች መሆናቸው ነው የተጠቆመው። በእነዚህ ቦታዎች የምርትና የጥሬ ዕቃ ችግር የሌለና የግብርና ኖራ ዋጋም በኩንታል እስከ 350 ብር እየተሸጠ ነው ብለዋል። የአፈር አሲዳማነት በረዥም ጊዜ የተፈጥሮ መዛባት ሂደት ውስጥ የሚከሰት እንደመሆኑ መጠን አንዴ ችግሩ ከተከሰተ በኋላ መፍትሔ በመስጠት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ወጪ እና ርብርብ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም ችግሩ ከመከሰቱ በፊት የአፈር አሲዳማነትን ለመከላከል የሚያስችሉ እርምጃዎችን መውሰድ ተገቢነት ያለው ጉዳይ እንደሆነ ነው የተጠቆመው፡፡ መንግሥት በያዘው የሌማት ትሩፋትና የግብርና ኢኮኖሚ አቅጣጫ በተለይም የስንዴ ምርት ከራስ ፍጆታ አልፎ ለሌሎች አገራት ምርቱን በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት በሚደረገው ጥረት የአፈር ምርታማነትን/ጤንነቱን መጠበቅ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑ የግድ ነው። “ለም አፈር በሌለበት ምርትና ምርታማነት የማይታሰብ ነው” የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ ግብርና የመሪነት ተግባሩን እንዲወጣ በቅድሚያ የአፈር ጤንነት ሊጠበቅ ይገባል ብለዋል። በመሆኑም ከዚህ በፊት ያለውን የግንዛቤ ችግርና ከአመራሩ እስከ አርሶ አደሩ ያለውን ክፍተት በመቅረፍ ችግሩን ለመቀነስ እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል። ሁሉንም ነገር ከመንግሥት መጠበቅ የለብንም የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ በቅድመ-መከላከል ሥራ ችግኝ በመትከል፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ በማከናወን፣ በተፈጥሮ ማዳበሪያ (ኮምፖስት) የራስን ማሳ በመንከባከብ፣ አማራጭ ሰብሎችን እያፈራረቁ በመዝራት፣ አሲዳማነትን መቋቋም የሚችሉ ተክሎችን በመምረጥ ማልማት እንዲሁም የግብርና ኖራ በመጠቀም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አብራርተዋል። በሀገራችን በተለያዩ የምርምር ተቋማት የተሰሩ ምርምሮች እንደሚያሳዩት አሲዳማ አፈርን ለማከም የተፈጥሮ ማዳበሪያዎችን ከኖራ ጋር አቀናጅቶ በመጠቀም በዋና ዋና ሰብሎች ላይ እስከ ሁለት እጥፍ የምርት ጭማሪ ማግኘት እንደሚቻል ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በመሆኑም አርሶ አደሮች ኖራ በግዥና በብድር የሚያገኙበትን ሥርዓት በተጠናከረ አግባብ መተግበር ያስፈልጋል። ልክ እንደ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በግዥ ወይም በብድር የግብርና ኖራ በማቅረብና በአሲዳማነት የተጎዳው መሬት እንዲያገግም ማድረግ ላይ አትኩሮ መስራት ሌላው የመፍትሄ አካል ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል። የእርሻ መሬት አያያዝና እንክብካቤ ጉዳይ የህግ ማዕቀፍ ኖሮት በዚያ አግባብ ተግባራዊ ማድረግም በተለይ በአሲዳማነት የመጠቃት አዝማሚያ የተጋረጠበትን የእርሻ መሬት ለመታደግና የተጎዳውንም እንዲያገግም ለማከም የሚሰሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ያስፈልገዋል። ከዚህ ባለፈም በአንድ የእርሻ ቦታ ላይ የተለያዩ ሰብሎችን መዝራት፣ አፈር ውስጥ ህይወት ያላቸው ነገሮች እንዲኖሩ ማድረግና የአፈሩን እርጥበታማነት ማዝለቅ ተገቢ ይሆናል።            
አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታና አብሮነት
May 3, 2023 931
በጣፋጩ ሰለሞን አገራችን ኢትዮጵያ የተለያየ ቋንቋ፣ ባህልና እምነት ያላቸው በርካታ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ተቻችለው፣ ተከባብረው፣ ተዋደው፣ በአንድነትና በአብሮነት በፍቅር የሚኖርባት አገር ነች። በዚህም የብሄር ብሄረሰቦች ሙዝዬም ነች የሚል አድናቆትን ተጎናፅፋለች-ኢትዮጵያ። እነዚህ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች የራሰቸው መገለጫ የሆኑ ቱባ ባህል አላቸው። ኢትዮጵያውያን ለዘመኑ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጥበብ መሰረት የሆኑ የአያሌ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤቶች ናቸው። ባህላዊ የመድኃኒት ቅመማና የህክምና ጥበብ ኢትዮጵያ ለዓለም ካበረከተቻቸው ትሩፋቶች መካከል አገር በቀል ዕውቀቶች ተጠቃሽ እንደሆኑ የታሪክ ድርሳናትና ሌሎች የየዘርፉ ተጓዳኝ መረጃዎች ያስረዳሉ። በተለይ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የተጠቀሙባቸውና እየተጠቀሙባቸው ያሉ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሌሎችም ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀሱ ናቸው። በጂንካ ዩኒቨርስቲ 5ኛው አገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ ሰሞኑን ተካሂዷል። በኮንፈረንሱ በአገር በቀል ግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም፣ለአብሮነት ትስስር እና ለአገራዊ ዕድገት ያላቸው ሚና የሚል እሳቤን ዓላማ ያደረገ ጥናት ቀርቧል። ጥናቱ እ.ኤ.አ ከ2018 እስከ 2022 ባሉ ዓመታት በመስቃን እና በማረቆ ህዝቦች ባህላዊ የግጭት አፈታት ላይ መሰረት አድርጎ የተካሄደ ነው። ጥናቱን ያካሄዱት "አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሰላም፣ ለፀጥታ እና ለዕድገት ያላቸው አስተዋፅኦ፤The Role of Indigenous conflict resolution Mechanism for peace,Security ,and Sustainable Development in Ethiopia " በሚል ርዕስ ያካሄዱት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ ዮሐንስ ተስፋዬ ናቸው። የጥናቱ ግኝት እንደሚያመለክተው ዘመናትን ተሻግረው እዚህ የደረሱ የሰላም ግንባታና ማጠናከሪያ የሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች አሁን ለደረስንበት ሳይንሳዊ ጥበብ መጎልበት እያገለገሉ ነው። የጥናት አቅራቢው ለኮንፈረንሱ ታዳሚዎች እንዳብራሩት ጥናቱ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ለአብሮነትና ለዕድገት አይተኬ ሚና አላቸው። እነዚህን አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች በአግባቡ መጠቀም ይገባል። እሳቸው እንዳብራሩት በአገራችን ሶስት አይነት የግጭት አፈታት ዘዴዎችን እንጠቀማለን። የወንጀልና የፍትሐብሔር ህጎች፣ እንደ ሽምግልና ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች እና ከሃይማኖታዊው ደግሞ ሸርዓ ከምንጠቀምባቸው የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ናቸው። ተመራማሪ ዮሐንስ እንዳሉት ጥናቱ በተካሄደበት በጉራጌ ዞን በመስቃን እና በማረቆ መካከል አጋጥሞ የነበረውን አለመግባባት ከመፍታት አኳያ ከዘመናዊ እውቀቶች ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ትልቅ ሚና ነበራቸው። በመስቃን እና በማረቆ ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት ከመስቃን፤ ከማረቆ እንዲሁም ከአጎራባች የኦሮሚያና ስልጤ ዞኖች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ተሳትፈዋል። በመስቃን እና በማረቆ መካከል ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት የተሳተፉት የሀይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች ግጭቱን ለመፍታት የተጠቀሙት ጥበብ አገር በቀል ዕውቀቶች በዘመናዊ ህግና አሰራር የማይቻሉትን የመፈጸምና ማህበራዊ አንድነትን ከማጠናከር አንፃር ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የጥናቱ ግኝት አመላክቷል። አለመግባባቱን ለመፍታት 26 ዙር ለመሸምገል ተቀምጠዋል። በማሸማገሉ ሂደት የተሳተፉት የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሁለቱን ማህበረሰቦች ለማቀራረብና በአካባቢው እረቀ-ሰላም ለማወርድ የከፈሉት መስዋዕትነት ቀላል አለመሆኑን በአጽኖኦት አስረድተዋል። የትኛውንም ውጣ ውረድና ጫና ተቋቁመው ሳይታክቱ ችግሩን የፈቱበት መንገድ ለዘመናዊው አስተዳደር ትምህርት የሚሰጥና በቅርስነት ለትውልድ የሚተላለፍ ሰናይ ተግባር መሆኑንም አስረድተዋል። ግጭቶች ቀደም ሲል የነበሩ፣ አሁንም ያሉና ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው። በተለያዩ ምክንያቶች የሚያጋጥሙ ግጭቶችን ፖለቲካዊ ትርጉም በመስጠት ከማጦዝ ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ተጠቅሞ ለማርገብ መስራት አዋጭና ተመራጭ መንገድ መሆኑን የጥናቱን ግኝት ዋቢ አድርገው ተመራማሪ ዮሐንስ መክረዋል። ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ለአገር በቀል እውቀቶች ተገቢውን ዕውቅና መስጠት ይገባል። አገር በቀል ዕውቀቶችን በትምህርት ሥርዓት ውስጥ አካቶ ለማጎልበት የተጀመረው አበረታች ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል። አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ አብሮነትን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው ያሉት ደግሞ የጂንካ ዩኒቨርስቲ የባህል ተመራማሪና የዩኒቨርስቲው የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ኤሊያስ ዓለሙ ናቸው። አክለውም ዘመናዊ ሕግን ተከትሎ በሚሰጡ ብያኔዎች አንዱ ወገን የሚደሰትበት ሌላኛው ደግሞ ቅር ተሰኝቶ የሚከፋበት ናቸው ይላሉ። በማህበራዊ ሸንጎ ግን ሁለቱም ወገን የሚደሰቱበት፣ ከልብ ይቅር ተባብለው ችግሮቻቸውን የሚፈቱበትና ዘላቂ እርቀ-ሰላም የሚያወርዱበት እንደሆነም ያስረዳሉ። ዶክተር ኤሊያስ አክለውም ይህም ማህበራዊ አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው የላቀ ነው። የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን ለመፍታትና በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በአገራችን ቱባ ባህሎች ውስጥ ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን መጠቀም ይገባል። በባህላዊ እሴቶቻችን ውስጥ ያሉ አገር በቀል ዕውቀቶች ቀጣይነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ እንዲውሉና ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆኑ ዕውቅና መስጠት፣ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ማካተት፣ በአግባቡ አደራጅቶና ሰንዶ ለትውልድ ማስቀመጥ እንደሚገባ አመላክተዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራን የሚጠበቅብንን ኃላፊነት በአግባቡ ልንወጣ ይገባል ይላሉ። አቶ መምህሩ ገዙሜ በጂንካ ዩኒቨርስቲ በሶሻል አንትሮፖሎጂ የትምህርት ክፍል የሶሽዮሎጂ መምህር ናቸው። አገር በቀል ዕውቀቶች ለአገራዊ ችግሮቻችን መፍቻ መንገዶች ናቸው ይላሉ። የሳይንሳዊ ምርምሮች ፅንሰ-ሀሳብ መነሻው አገር በቀል ዕውቀቶች እንደሆኑ ይጠቅሳሉ። በአገራችን በርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ቢኖሩም እንዳለመታደል በአግባቡ መጠቀም አልቻልንም ሲሉም ያክላሉ። እሳቸው እንዳሉት መንግሥት አሁን ለአገር በቀል ዕውቀቶች የሰጠው ዕውቅና ለአገር በቀል ዕውቀቶች መጎልበትና ጥቅም ላይ መዋል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ይህን ዕድል በመጠቀም አገር በቀል እውቀቶች ጎልተው እንዲወጡና በትምህርት ሥርዓቱ ተካተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት ይገባል። በተለይ የማህበረሰቡ የግጭት አፈታት ዘዴና በምክክር ችግሮችን የመፍታት ጥበብ የታሰበው አገራዊ የምክክር መድረክ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። በመሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ፣ ለኢትዮጵያውያን የአብሮነት ትስስርና መስተጋብር መጠንከር እንዲሁም ለአገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና እጅግ የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ተገንዝቦ ተገቢውን ዕውቅና በመስጠት መጠቀም ይገባል።
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ
Apr 2, 2023 1449
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ በሰለሞን ተሰራ በታሪክ ተመዝግበው የምናገኛቸው አያሌ መልካምና በጎ ነገሮች የመኖራቸውን ያህል በተቃራኒው ደግሞ የሰው ልጆች ግፍና በደል ሲፈጽሙና ሲያስተናግዱ ኖረዋል። በዚህም በተለይ በበደሉ ገፈት ቀማሾች ላይ የሚደርሰው ድንጋጤ፣ ሰቆቃና ሀዘን ሰዎችን ለበቀል እያነሳሳ ሌላ ጥፋት ሲያስከትል ማስተዋልም እንግዳ ነገር አይደለም። በዚያው ልክ ሰዎች የደረሰባቸውን ግፍና መከራ ለማራገፍ ፍትህን ሲሹና ሲጠይቁ ይስተዋላል። እምባቸው የሚታበሰው፣ ቁስላቸው የሚሽረው ለደረሰባቸው በደል ካሳ የሚሆን ፍትህ ሲያገኙ ብቻ እንደሆነም ያምናሉ። በርካታ አገራትም በታሪክ ውስጥ ላጋጠሟቸው ስብራቶች የሽግግር ፍትህን አማራጭ አድርገው በመጠቀም ለችግሮቻቸው መፍትሄ ያበጃሉ። እኤአ በ1970 ዎቹ መጀመሪያ በምስራቅ አውሮፓ እና ደቡብ አሜሪካ ተግባራዊ በተደረገው የሽግግር ፍትህ በጦርነትና በግፍ አገዛዝ የተበደሉ አካላት ፍትህ እንዲያገኙ የተደረገበት መንገድ ተጠቃሽ ነው። ከዚህ ጊዜ በኋላ የሽግግር ፍትህ በተለይ በመደበኛ የህግ ስርአት ብቻ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስቸግሩ ጉዳዮችን ጭምር በተጠያቂነት፣ በይቅርታ፣ በካሳ ወዘተ መፍትሄ በመስጠት የፍትህ ማስፈኛ መንገድ ተደርጎ ተወስዷል። የሽግግር ፍትህ ማለት በማህበረሰቡ ውስጥ በስፋት ለተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ምላሽ የሚሰጥበት አካሄድ መሆኑን ምሁራን ያስረዳሉ። ይህንን ሂደት ሰላማዊ፣ አካታችና ተደራሽ ለማድረግ የሁሉም ጥረትና አጋርነት ቀዳሚ መነሻ ሊሆን እንደሚገባውም ይገልጻሉ። የሽግግር ፍትህ በአንድ ጊዜ የሚያልቅ ሳይሆን ጊዜ የሚጠይቅና ዓመታትን ሊወስድ የሚችል ነው። ይህም ለተበዳዮች ፍትህ በመስጠት፣ ካሳ በመክፈል፣ የወደሙ ንብረቶችን መልሶ በመገንባትና በመሰል ሂደቶች ሊፈጸም ይችላል። የሽግግር ፍትህ ሀገራት ከብጥብጥ፣ ከፀብና ጥላቻ አዙሪት እንዲወጡ በማድረግ በኩል የማይተካ ሚና እንዳለው የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮዎች ያሳዩናል። በ2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ የፀደቀው የአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ማዕቀፍ፣ የሽግግር ፍትህ ሀገራት የተለያዩ መደበኛ እና ባህላዊ ወይም መደበኛ ያልሆኑ የፖሊሲ እርምጃዎችንና ተቋማዊ አሠራሮችን በመጠቀም የተፈጸሙ ጥሰቶችን፣ ክፍፍሎችንና አለመመጣጠኖችን ለማስወገድና ለደኅንነትም ሆነ ለዴሞክራሲያዊና ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሥርዓት ግንባታ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የሚደረግ ጠቃሚ እና አስፈላጊ ሂደት እንደሆነ ይገልጻል። የሽግግር ፍትህ በግጭት፣ በጦርነት ወይም ጨቋኝ ሥርዓት በነበረበት ወቅት ለተፈፀመ ጥቃት፣ መጠነ-ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና በደል የተሟላ መፍትሄ መስጠት መቻል ነው። ይህም በዋናነት ሙሉ ፍትህ የሚሰጥበትን መንገድ በመዘርጋት ዘላቂ ሰላም፣ እርቅ፣ መረጋጋት እና የህግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት መገንባት የሚቻልበትን ሁኔታ የሚመለከት ነው። በኢትዮጵያ ተግባራዊ ሊደረግ የታሰበውና በፖሊሲ አማራጭ ዝግጅት ሂደት ላይ የሚገኘው የሽግግር ፍትሕ በአራት ዋና ዋና ምክንያቶች አስፈላጊ መሆኑን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል። አንደኛው ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሀገራዊ አውድ ሲሆን በዚህም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ አለመረጋጋት፣ ግጭትና የእርስ በርስ ጦርነት ተከስቷል። ይህም ዜጎችን ለሞት፣ ለአካል ጉዳት፣ ለመፈናቀል ያጋለጠ መሆኑ በገፊ ምክንያትነት ይጠቀሳል። ለነዚህ ችግሮች ከዚህ በፊት የተሰጡ ምላሾች ሙሉ አለመሆናቸው የአጥፊዎችና የተጎጂዎችን ቁጥር ማብዛቱ፣ የበደሎች መደራረብ እና የጥፋቶች ማህበረሰባዊ ቅርጽ መያዝ በመደበኛው የፍትሕ ሥርዓት እና አካሄድ ፍትሕ መስጠትንም ሆነ ይቅርታ እና እርቅን ማከናወን አላስችል ማለቱ የሽግግር ፍትህ ትኩረት እንዲሰጠው አድርጓል። ሁለተኛው የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ማለትም ባለፉ በደሎች ይቅር ለመባባል፣ እርቅ ለማውረድ፣ ሕዝብ ለማቀራረብ፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እና ለተፈጸመ በደል እውቅና ለመስጠት አስፈላጊ በመሆኑ ነው። ሶስተኛው ምክንያት የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ሂደት ሳይተገበር የዴሞክራሲ ሽግግርም ሆነ ዘላቂ ሰላም ማስፈን አይቻልም የሚል ነው። የመጨረሻው በገፊ ምክንያትነት የሚጠቀሰው ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እና የሕግ የበላይነትን ለማስፈን የሽግግር ፍትህ ወሳኝ በመሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በነዚህ ምክንያቶች የሽግግር ፍትሕን ለማስፈን እየሰራች መሆኑ በበርካቶች ዘንድ በአዎንታዊ መልክ ይጠቀሳል። በተለይ የሽግግር ፍትህን ተግባራዊ ካደረጉ አገራት ተሞክሮ በመውሰድ ለውጤታማነቱ ከተሰራ በርግጥም አይነተኛ መፍትሄ ነው። ከአፍሪካ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ በቅርቡ ደግሞ ጋምቢያ የሽግግር ፍትህን ለችግሮቻቸው መፍቻነት ከተጠቀሙ አገራት መካከል ናቸው። ሩዋንዳ ሩዋንዳ እኤአ በ1994 በመቶ ቀናት ብቻ ከነበሯት 7 ሚሊዮን ዜጎቿ 800 ሺዎቹን በግፍ ተነጥቃለች። 2 ሚሊዮን የሚጠጉት በስደት ሀገራቸውን ለቀው ሲወጡ በዚህ የጭካኔ ተግባር ተሳትፎ ነበራቸው የተባሉ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ላይ ክስ በመመስረት ፍትህ ፊት አቅርባቸዋለች። በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት በሀገር ውስጥ ችሎትና በባህላዊ መንገድ በተዳኙት ወንጀለኞች ላይ የተሰጡት የፍትህ ውሳኔዎች አሁን ላይ ሀገሪቱን በዲሞክራሲና በሰላም እንዲሁም በብልፅግና መንገድ መራመድ እንድትችል አድርጓታል። ሩዋንዳውያን በቆየ ሀገራዊ ብሂላቸው ”ሁላችንም የአንድ አባትና እናት ልጆች ነን ይላሉ”። ይህንኑ ብሂል መመሪያቸው በማድረግ በሀገሪቱ ያሉት “ቱትሲ” እና “ሁቱ” የተባሉት ዋነኛ ብሄሮች በአብሮነት ለዘመናት ኖረዋል። ሩዋንዳ በጀርመን የቅኝ አገዛዝ ስር እንደወደቀች የዘር ልዩነቱን ወደፊት ያመጡት ቅኝ ገዥዎች ሁለቱን ብሄሮች የሚያጋጩ ሴራዎችን በመጎንጎን ቱትሲዎችን መግደል የፖለቲካቸው ስልት ማስፈጸሚያ አደረጉት። ይህ ከፋፋይ የፖለቲካ ሴራ በቤልጂየም የእጅ አዙር አገዛዝ ዘመንም እንደቀጠለ ይነገራል። በዚህም ማንነትን መሰረት ያደረገ የፖለቲካ አደረጃጃት፣ የመታወቂያ ወረቀት፣ ቱቲስዎችን በስልጣን ወደፊት ማምጣትና ሁቱዎችን አሳንሶ መመልከትን ባህል አደረጉት። በዚሁ መርዘኛ ሀሳብ መነሻነት ከነጻነት በኋላ እኤአ ከ1959 እስከ 1967 አካባቢ በመንግስት በተደገፈ የዘር ማጥፋት 20ሺ የሚጠጉ ቱትሲዎች ሲገደሉ 300ሺ የሚጠጉ ሀገራቸውን ለቀው ተሰደዱ። በዚህም እኤአ በ1987 በቱትሲዎችና ለዘብተኛ ሁቱዎች የተቋቋመው የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር እኤአ በ1993 የመንግስትን ስልጣን ለመጋራት በቃ። ነገር ግን እኤአ በሚያዚያ 6 ቀን 1994 የሀገሪቱ መሪ የነበሩት ሃባይሪማና በቅጥረኞች በመገደላቸው በሀገሪቱ አመጽ እንዲቀጣጠል ምክንያት ሆነ። ይህን ተከትሎ “ኢንተርሀሞይ” በመባል የሚጠራው የሚሊሽያ ቡድን በቱትሲዎችና በለዘብተኛ ሁቱዎች ላይ ዘመን የማይሽረው ግፍና ጭካኔ በመፈጸም 800ሺ የሚጠጉትን ከምድር ላይ ለዘለአለሙ አሰናብቷቸዋል። ይህ ደግሞ የዘር ማጥፋት ወንጀል በመሆኑ አጥፊዎቹ በተለያዩ የፍትህ አደባባዮች ተከሰው ቅጣታቸውን ለመቀበል በቅተዋል። ነገር ግን ይህ ብቻውን በህዝቡ ውስጥ ስር የሰደደውን ቁስል እንዳማይሽረው በመታመኑ ሩዋንዳ የሽግግር ፍትህን በመከተል አመርቂ ስራ ሰርታለች። በተለይም ክስና ይቅርታ ትልቅ ቦታ ነበራቸው። በክስ ሂደቱ ሁሉንም ተጠያቂ ማድረግ ቢከብድም በዋናነት ተሳታፊ የነበሩትን በመለየትና ተጠያቂ በማድረግ ፍትህ እንዲሰፍን ተደርጓል። መንግስት ውጫዊና ውስጣዊ ግፊት ቢበዛበትም ከፍተኛ ግፍ የፈጸሙትን በመለየት እንዲቀጡ አድርጓል። ይቅርታውንም በተጠና መንገድ በማከናወን ለጥቂቶች ምህረት አድርጓል። በጊዜ ሂደት የእስራት ጊዜአቸውን ላገባደዱ፣ ለአዛውንቶች፣ ለታማሚዎችና ለወጣቶች ምህረት በማድረግ ቁርሾው እንዲሽር ተደርጓል። ምህረት የተደረገላቸው ሰዎች ስለብሄራዊ እርቅ፣ አብሮነት፣ ሀገራዊ ማንነትና ሰብዓዊ ክብር እንዲማሩ በማድረግ እርቁን ሙሉ ማድረግ ተችሏል። የሩዋንዳ የሽግግር ፍትህ በዋናነት እውነትን ማፈላለግ፣ ነገሮችን መልሶ ማስታወስ ወይም የመታሰቢያ ቦታዎችን በመመስረትና ቀን በመሰየም ሁኔታው ታስቦ እንዲውል ማድረግ፣ መልሶ ማቋቋምና እርቅ ማውረድ የተቋማት ማሻሻያ ማድረግ ላይ ያተኮረ ነበር። ሴራሊዮን እኤአ ከ1991 አስከ 2002 የዘለቀው የሴራሊዮን የእርስ በርስ ግጭት በትንሹ የ100ሺ ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ አልፏል። ሌሎች በ100ሺ የሚቆጠሩ ዜጎችን ለከፋ የአካል ጉዳት፣ ድህነትና የአዕምሮ መቃወስ ዳርጓል። ግጭቱ የተጀመረው ራሱን “የተባበሩት አብዮታዊ ቡድን” ብሎ በሚጠራው የታጣቂዎች ስብስብ ሲሆን በወቅቱ ቡድኑ በላይቤሪያ መንግስት ይደገፍ እንደነበር ይነገራል። የተቃውሞአቸው መነሻ ደግሞ የመንግስት ብልሹ አስተዳደር፣ የገጠሩ ማህበረሰብ ከኢኮኖሚና ፖለቲካ ተሳትፎ መገለል እና መጠነ ሰፊ የህግ ጥሰቶች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ። የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሃብት በተለይም የአልማዝ ማዕድኗን በህገወጥ መልኩ ሲበዘብዙ የነበሩ አመራሮች ቁርሾውን በማባባስ ህልውናቸውን ለማስቀጠል ቢጥሩም እኤአ በ2002 በተደረሰ የሰላም ስምምነት ከ 76 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን በማስረከብ ህብረተሰቡን እንዲቀላቀሉ ተደርገዋል። በዚያው ዓመት የሴራሊዮን የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን የተቋቋመ ሲሆን በተመሳሳይ የሴራሊዮን ልዩ ችሎት ተመስርቷል። ሴራሊዮን በእርስ በርስ ግጭት ውስጥ በነበረችባቸው 12 ዓመታት አራት መፈንቅለ መንግስት የተካሄደባት ሲሆን የስልጣን መንበሩን የተፈራረቁበት የተለያዩ ወታደራዊ አመራሮች ለችግሩ መፍትሄ ከማበጀት ይልቅ በቤንዚን ላይ እሳት የሚያርከፈክፉ ሆነው ታይተዋል። በሴራሊዮን ለደረሰው እልቂት እኩል ኃላፊነት የሚወስዱት መንግስትና ታጣቂዎች በወቅቱ ሴቶችን በመድፈር፣ ህፃናትን በግዳጅ ለጦርነት በመመልመል፣ ንብረት በማውደምና በ100ሺ ለሚቆጠሩ ሰዎች መሞት ተጠያቂ ተደርገዋል። ከዚህ ባለፈ በቅድሚያ ታጣቂዎችን የጦር መሳሪያ ለማስፈታት የተሄደበት ርቀት ለሰላም መስፈን ትልቅ እገዛ ማድረጉ የሚገለጽ ሲሆን ከ70 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎችን መሳሪያ ማስፈታት መቻሉ ግጭቱን ለማስቆም በራሱ ታላቅ ስኬት ነበረው። በወቅቱ ግፉን የፈጸሙት ታጣቂዎች በመንግስት ቅጣታቸውን እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን ህብረተሰቡም ወንጀለኞችን ከማህበረሰቡ በማግለል የስነ ልቦና ቅጣት እንደጣለባቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በዚህም ታጣቂዎቹን ወደ ህብረተሰቡ መልሶ ለመቀላቀል የተደረገው ጥረት በፈተና ቢታጀብም በህዝቡ ይሁንታ ውጤታማ ሆኗል። በሴራሊዮን የሽግግር ፍትህን ለማስፈን የተቋቋሙት የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን፣ የሴራሊዮን ልዩ ፍርድ ቤት፣ በፀጥታ ተቋማት ላይ የተደረገው ማሻሻያ፣ የመልሶ ማቋቋምና የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ምስረታ ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው። የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን በተሰጠው ስልጣን መሰረት ተጎጂዎችን ከሰቆቃ መታደግና ችግሩን በዕርቅ መፍታት፣ ብዙሀኑ ላይ ለደረሰው ግፍ ምላሽ መስጠት፣ ግፉ በቀጣይ እንዳይደገም መፍትሄ ማበጀት ላይ አተኩሮ ሰርቷል፡፡ በዚህም ከተጎጂዎች ቃለ ምልልስ በመነሳት በደረሰበት ድምዳሜ የመንግስት አካላት የመልካም አስተዳደር መጓደል፣ ሙስና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ከነፃነት በኋላ የነበረው አመራር ብቃት ማነስ ለብጥብጡ መንስኤ እንደሆነ አመላክቷል። ልዩ ፍርድ ቤቱም በቅድሚያ ተጎጂዎችን ሰብስቦ በማናገር እንዲሁም የሲቪል ማህበራትን ህብረተሰቡንና መገናኛ ብዙሃንን በማካተት ሁሉንም የሚያስማማ ውሳኔ በመስጠት ችግሩ ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ መፍትሄ እንዲያገኝ አስችሏል። የመልሶ ማቋቋም ሂደቱ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበርና ልዩ በጀት በመመደብ የተከናወነ ሲሆን የተጎጂዎችን ሰቆቃ ሊጠግን በሚችል መልኩ መተግበሩንም ብዙዎች ይመሰክራሉ። በዚህም ተጎጂዎች ነፃ የጤና አገልገሎት፣ ትምህርት፣ መኖሪያ ቤትና መቋቋሚያ እንዲያገኙ ተደርጓል። በአብነት የተነሱት የሩዋንዳና ሴራሊዮን ተሞክሮዎች የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭቶችን ያስተናገዱ ሀገራት የተሻለ ነገን እንዲገነቡ ሁነኛ መፍትሔ ስለመሆኑ አመላካች ናቸው። በተመሳሳይ የሽግግር ሂደት ያለፉና ተሞክሮ ያላቸው የደቡብ አፍሪካ እና ጋምቢያ ምሁራንም ይህንኑ እውነት የሚያረጋግጥ ሀሳባቸውን ለኢዜአ ሰጥተዋል። በደቡብ አፍሪካው ፍሪታውን ዩኒቨርሲቲ የፍትሕና ዕርቅ ኢንስቲትዩት ኃላፊ እና በአፍሪካ ጥናትና ምርምር የካበተ ልምድ ያላቸው ፕሮፌሰር ቲም ሙሪቲ በአፍሪካ ሽግግር ፍትህ ዙሪያ ጥልቅ ምርምር አድርገዋል። ኢትዮጵያ ታሪካዊና የአፍሪካ ተምሳሌት ሀገር ናት የሚሉት ፕሮፌሰሩ፤ የገጠማትን ችግር ለመፍታት የሽግግር ፍትህ ሂደት መጀመሯን አድንቀዋል። የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭትና ግፎችን ባሳለፉ ማህበረሰቦች ትናንትን በይቅርታ የነገውን ተሰፋ ለመሻገር አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን በማንሳት ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ፣ ባርነት እና ቅኝ ግዛት የጭቆና ስርዓት ነጻ ስትወጣ ስርዓቱ በጥቁሮች ላይ ለፈጸመው ግፍ፣ መገለልና ብዝበዛ መፍትሄ ለመስጠት ሽግግር ፍትህ ሂደት መተግበሩን ይጠቅሳሉ። ፕሮፌሰር ሙሪቲ፤ የወቅቱ ፕሬዝዳንት ኔልሰን ማንዴላ በጥቁሮች ላይ የተፈጸሙ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት መልክ ለመስጠት ብሎም ህዝባዊ አብሮነት እንዲቀጥል በሊቀጳጳስ ዴዝሞንድ ቱቱ መሪነት የዕውነትና ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን መቋቋሙን ያስታውሳሉ። የሽግግር ፍትሕ ሂደቱ ከአፈጻጸም ጋር የተያያዙ ክፍተቶች ቢኖሩበትም አካታችና የአገሪቱን የቀጣይ ጉዞ ለመቀየስ መሰረት የጣለ እንደነበር ገልጸዋል። ይህም ኢትዮጵያ ተሞክሮ ልታደርገው የምትችለው ነው ይላሉ። በጋምቢያ በቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ያህያ ጃሜህ ዘመነ መንግስት ለ22 ዓመታት የተፈጸሙ ግፎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት የፈቱት የዕውነት፣ ዕርቅና ካሳ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ጋምቢያዊው ዶክተር ባባ ጋሌህ ጃሎው፤ የሽግግር ፍትህ አስፈላጊነት በተለይም ኢትዮጵያን ለመሰሉ ሀገራት አጠያያቂ አለመሆኑን ይላሉ። በተመሳሳይ በጋምቢያ አምባገነን መንግስት የተፈጸሙ በደሎችን መልክ ለማስያዝ የተቋቋመው የዕውነት፣ ዕርቀ ሰላምና ካሳ ኮሚሽን ዜጎች ዕውነቱን እንዲረዱ፣ በዳዮች እንዲጠየቁና ተበዳዮች እንዲካሱ የሚያስችል ሰነድ ለሀገሪቷ መንግስት ማቅረቡን ዶክተር ባባ ጋሌህ ይገልጻሉ። እነዚህ ምሁራን ኢትዮጵያ ለማድረግ ያሰበችው የሽግግር ፍትህ ሂደት ከአፍሪካ ሕብረት የሽግግር ፍትሕ ፖለሲ እና የሀገራትን ልምድ የቀመረ፣ አካታች፣ ተበዳዮችን የሚክስና ሀገርና ህዝብ ወደፊት በሚያሻግር አግባብ እንዲፈጸም አስተያየታቸውን ጠቁመዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራኑ ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ለሚመለከተው አካል እንደሚያጋሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያን ባለፉት ጥቂት ዓመታት በህዝቦች የተባበረ ክንድ ለውጥ በማምጣት አዲስ ምእራፍ የጀመርንበት፣ አዲስ መንግስት ስልጣን ተቀብሎ ያለፉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በይፋ በማመን ይህንኑ ለማሻሻል ቃል የገባበት፣ የዲሞክራሲ ሽግግር ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት የተጀመሩበት እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት የደረሱ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ለማለፍ መንገድ የጀመርንበት ወቅት ላይ መሆናችን ይታወቃል። የሽግግር ፍትህ የተበዳዮችን እምባ ከማበስ ባለፈ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ በማስቀመጥ ከቂም በቀል የጸዳ ትውልድ ለመፍጠርና ለአገረ መንግስት ግንባታ በጋራ ለመሰለፍ መፍትሄ መሆኑን ከላይ የተጠቀሱት አብነቶች ምስክሮች ናቸው። ለአፍሪካ ጉዳዮች አፍሪካዊ መፍትሄን የምታስቀድመው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገራት ተሞክሮዎችን በመቀመር፣ ካለፈችባቸው መንገዶች ትምህርት በመውሰድ፣ ውጤታማ የሆነ የሽግግር ፍትህ ስርዓትን እውን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል። የሽግግር ፍትሕ በተለይም በሽግግር ላይ ያሉ ሀገራት ህዝቦች ከነበሩበት ግጭት እንዲሁም ከደረሰባቸው ግፍ እና ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ወጥተው ወደ አዲስ ሰላማዊ እና አብሮነት ጉዞ ለመጀመር የሚደረግ የፍትሕ ክዋኔ አይነት በመሆኑ በትኩረት ሊሰራበት ይገባል።          
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 2381
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
ትንታኔዎች
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች
May 26, 2023 139
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች ሰለሞን ተሰራ አውሮፓዊያን ለጥቁሮች ከነበራቸው ዝቅተኛ አመለካከት በመነጨ እብሪት “የአፍሪካ ቅርምት” እየተባለ በሚታወቀው አጀንዳቸው አህጉሪቱን ለመከፋፈል ቁጭ ብለው የመከሩት በ18ኛው ክፍለ ዘመን ማገባደጃ ላይ ነበር፡፡ በጀርመን መዲና በርሊን የተሰበሰቡት ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ፖርቱጋል፣ ቤልጂየም እንዲሁም ዘግይተው የተቀላቀሉት ጣልያን እና ጀርመን አቅማቸው የፈቀደውን ያህል አህጉሪቱን በመቆጣጠር ሀብቷን ለመመዝበር ሕልም አንግበው የወል ቃል ገብተዋል፡፡ እነዚህ ሀገራት አፍሪካን አንድ አድርጎ ለመግዛት ሕልማቸውን አስተሳስረው ቢነሱም በመሀከላቸው በነበረው ፉክክር የተነሳ ምኞታቸው ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡ አውሮፓውያን በአህጉሪቱ የዘረጉትን የቅኝ አገዛዝ መዋቅር በጣጥሶ ለመጣል በቅድሚያ አህጉሪቱን አንድ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን የሚያምኑ አፍሪካውያን መሪዎች ህብረት ለመመስረት ቢነሱም ሀሳባቸው ለሁለት በመከፈሉ ሁለት ቡድን እንዲፈጠር ምክንያት ሆኖ አልፏል፡፡ ይህን ተከትሎ የተፈጠሩት ሁለት ቡድኖች በአንድ ወገን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ሀገራቱ በፍጥነት ተዋሕደው አፍሪካ አንድ ልትሆን ይገባል የሚለው የካዛብላንካ ቡድን፤ እንዲሁም አንድ ከመሆን በፊት ሌሎች ትብብሮች ሊቀድሙ ይገባል የሚለው የሞኖሮቪያ ቡድኖች ነበሩ፡፡ ሁለቱም ቡድኖች የአፍሪካ አንድነት እንዲመሰረት ጽኑ አቋም ቢኖራቸውም፣ እንዴት ነው መመስረት ያለበት የሚለው ጥያቄ ግን የልዩነታቸው ወሰን ሆኖ ወደ ንትርክ የገቡበት ጊዜ ነበር። በ1961 የተመሰረተው የካዛብላንካው ቡድን በጋናዊው ኩዋሜ ኑኩርማህ የሚመራ ሲሆን ዓላማቸው አፍሪካ አሁን መዋሃድ (አንድ መሆን) አለባት የሚል ሲሆን ከአባላቱ መካከል ጊኒ፣ ሊቢያ፣ ግብጽ፣ ሞሮኮ፣ ማሊ፣ አልጄሪያ ይገኙበታል። የሞኖሮቪያው ቡድን ደግሞ በሴኔጋላዊው መሪ ሴንጎር የሚመራ ሲሆን በስሩም ሃያ አራት ሃገራትን፣ ማለትም ናይጄሪያ፣ ሴኔጋል፣ ካሜሮን፣ አይቮሪኮስት፣ ቶጎ፣ ላይቤሪያ እና ሌሎች ብዙ የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበሩ ሃገራትን ያቀፈ ነበር፡፡ የዚህ ቡድን የውህደት መርህ ደግሞ “አፍሪካ መዋሃድ የምትችለው በኢኮኖሚያዊ ትብብር ሆኖ በቀስታ በምታደርገው ጉዞ ነው” የሚል ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ወገኖች ፍጥጫ አርግባ ወደ ውህደት ያመጣቻቸው ኢትዮጵያ ስትሆን ድርጅቱ የዛሬ 60 ዓመት እ.ኤ.አ ግንቦት 25 ቀን 1963 ሲመሰረት የመጀመሪያው ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት አጼ ኃይለስላሴ ነበሩ፡፡ የፓን አፍሪካኒዝም ልጅ የሆነው የያኔው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋና ዋና ዓላማዎቹ ቅኝ ገዢዎችን ማስወገድ፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል አንድነትና ሕብረትን ማበረታታት፣ ለአፍሪካዊያን የተሻለ ህይዎት እና እድገት ለማምጣት፣ ሉዓላዊነትንና የወሰን አንድነትን ማስጠበቅ፣ ሰብዓዊ መብቶችን ማስከበር፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል የሚካሄዱትን ግጭቶች በሰላማዊና በዲፕሎማሲ መፍታት የሚሉ ነበሩ። የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀደምት መሪዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን የሚተካ አዲስ አህጉራዊ ድርጅት ለመመስረት እ.አ.አ በ1999 ያሳለፉትን ውሳኔ መሠረት በማድረግ የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ በሐምሌ 2002 በደርባን ደቡብ አፍሪካ በይፋ መመስረቱ ይታወቃል። የአፍሪካ ኅብረት ራዕይም፤ የተቀናጀች፣ የበለጸገች እና ሰላማዊ፣ በራሷ ዜጎች የምትመራ እና በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ተፎካካሪ የሆነች አፍሪካን መመስረት ነው። እ.አ.አ በ2013 የአፍሪካ መሪዎች በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት አጀንዳ 2063 የተሰኘውን አህጉራዊ እቅድ ነድፈዋል። እቅዱ ከሁሉም በላይ በአህጉሪቱ ላይ የሚቃጡ ጦርነቶችን ማስቆምና መሰረተ ልማት ዝርጋታ ላይ የሚያተኩር ሲሆን በአህጉሪቱ ዜጎች ከአገር አገር ነፃ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ራዕይ የሰነቀ ነው። ሌላው ወሳኝ ፕሮጀክት የአፍሪካ ነፃ ገበያ ምህዳርን መክፈት ሲሆን ይህ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ በርካታ አገራትን አሳታፊ በማድረግ የዓለም ትልቁ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ ስምምነት ሲሆን አሁን ላይ ተግባራዊ ሊደረግ ከጫፍ ደርሷል። ይህ የነፃ ገበያ ስምምነት በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ለማስፋፋት የታለመ ከመሆኑ በላይ የሀገራቱን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድገው ታምኖበታል። የአፍሪካ ነፃ ገበያ ስምምነት አገራት የውስጥ ገበያቸውን ለመጠበቅ ባወጧቸው ቀደምት ህጎችና እንዲሁም በደካማ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ምክንያት ከፍተኛ ችግር እንደሚገጥመው አስተያየት ቢሰጥበትም ያዘለው ተስፋ ግን ከችግሩ የገዘፈ ነው። ሁሉንም የአፍሪካ አገራት መዲናዎች እና የንግድ ማዕከሎች በፈጣን የባቡር መስመር ማገናኘት፣ በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ማበረታታት እንዲሁም የአፍሪካ አገራት በዓለም አቀፍ የንግድ ገበያ ያላቸውን ተሳትፎ ማጎልበት አጀንዳ 2063 ካስቀመጣቸው ግቦች መካከል ቀዳሚዎቹ ናቸው። አፍሪካውያን በአህጉሪቱ በነፃነት የመዘዋወር፣ የመስራት እና የመኖር መብት እንዲኖራቸው ማድረግ እንዲሁም በአህጉሪቱ ያሉ ግጭቶችን ማስቆም እና ሌሎችም በርካታ ግቦች በእቅዱ ላይ ተቀምጠዋል። ነገር ግን የአፍሪካ ሕብረት እነዚህን አጀንዳዎች ለማስፈፀም በእጅጉ እየተፈተነ ሲሆን ለዚህ ዋነኛ መንስኤው የሕብረቱ አባል አገራት በገቡት ስምምነት መሰረት ነገሮችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ማስገደድ አለመቻሉ እንደሆነ ይነገራል። ተንታኞች እንደሚሉት የአፍሪካ አገራት ያለባቸውን ከፍተኛ የእዳ ጫና ለመክፈል የሚያደርጉት ትግል ትልቁን አህጉራዊ አጀንዳ ችላ እንዲሉ ግድ ብሏቸዋል። የህብረቱ በጎ ርምጃዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋነኛ ዓላማው በቅኝ አገዛዝ ስር የነበሩ ሀገሮችን ነጻ ማውጣት ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር የተሳካ ተግባር ማከናወኑ በታሪክ ሲወደስለት የሚኖር ስኬቱ ነው፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆኖ ከሞላ ጎደል ውጤት ያስመዘገበባቸው ዘርፎች አሉ። ሀ. ሰላምና ደህንነት የአፍሪካ ህብረት ሰላምንና ደህንነትን ለማረጋገጥ በተለይም የአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ኃይል በተለያዩ የአህጉሪቱ ክፍሎች ያደረገው ተጋድሎ በአዎንታ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ ለማሳያም ላይቤሪያ፣ ሴራሊዮን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን ተሰማርቶ የነበረው የአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ኃይል ከሌሎች የተሻለ አፈጻጸም እንዳለው ይገለጻል፡፡ ለ. ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በተለያዩ የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መረጋጋት እንዲፈጠር ለማድረግና ዴሞክራሲን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት እና የተፈጥሮ ሃብቷ ለፈጣን ዕድገቱ በምክንያትነት ይነሳሉ፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋና ኢኮኖሚው እንዲያድግ የወሰዳቸው ተቋማዊ እርምጃዎች ወሳኝ ሚና ሲኖራቸው የአፍሪካ ልማት ባንክን በማቋቋም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መደገፉ ተጠቃሽ ነው፡፡ በተለይም ለመንገድና ለውኃ ሃይል ማመንጫ ባንኩ ያደረገው ድጋፍ ተገቢው ቦታ የሚሰጠው ሲሆን ለአፍሪካ የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነት መሻሻል ማነቆ የሆኑትን ታሪፍ በመቀነስም የተሻለ ስራ ሰርቷል፡፡ ሐ. ዓለም አቀፍ ተሰሚነት የአፍሪካ ህብረት በዓለም አቀፍ መድረኮች በተለይም የዓለም ኢኮኖሚንና የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከተ አንድ አቋም መያዙ ከህብረቱ ታሪክ ተጠቃሽ ስኬቶች አንዱ ነው፡፡ አፍሪካ የአየር ንብረት ተፅዕኖውን ለመላመድና ለመቋቋም የሚረዳትን ተገቢውን ክፍያ እንድታገኝ ህብረቱ ውጤታማ ስራ ሰርቷል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ የልማት ችግሮችን ለመፍታት ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ጥረት አድርጎ ባስመዘገበው ውጤትም ይመሰገናል፡፡ በተለይም የተባበሩት መንግስታት የሚሊኒየም የልማት ግቦች እንደ መገለጫ ይነሳሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ለማግኘት እንዲሁም የአፍሪካ ድምጽ የሚጎላበት ሚዲያ እንዲኖር የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች በአዎንታ የሚነሱ ናቸው። መ. ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ ዴሞክራሲንና መልካም አስተዳደርን በማስፈን በኩልም ከነጉድለቶቹም ቢሆን በመልካምነት የሚጠቀሱ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይገለጻል፡፡ በአህጉሪቷ ከ30 ዓመት በፊት አምስት ሀገራት ብቻ ዴሞክራት የነበሩ ሲሆን አሁን ከአፍሪካ ሀገሮች 95 በመቶዎቹ ወቅቱን ጠብቀው ምርጫ የሚያካሂዱ ሀገራት ናቸው፡፡ የምርጫ ታዛቢዎችን በአባል ሀገራት እየላከ መታዘቡም እንደ ጥሩ ጅምር መታየት ያለበት ነው፡፡ በተለይ ደግሞ የአፍሪካ የእርስ በርስ መገማገሚያ መድረክን /APRM/ ማቋቋሙ በጥንካሬ ሲነሳ በዚህ መድረክ አማካኝነት ሀገራት በራሳቸው ተነሳሽነት ስለሀገራቸው የመልካም አስተዳደር አፈጻጻም ሪፖርት የሚያደርጉበትና ልምድ የሚለዋወጡበት እድል ተፈጥሯል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በሀገሮች ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ያለመግባት መርህ በማሻሻል በመፈንቅለ መንግስት የሚመጡ ቡድኖችን ላለመቀበል መወሰኑ ህብረቱ በዴሞክራሲ ላይ ያለውን አቋም ያሳያል፡፡ መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች በርግጥ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት አንግቦት ከነበረው አባል ሀገራቱን ከቅኝ ገዥዎች ነፃ የማውጣት ተልዕኮ አንስቶ እስከ ወቅታዊው የአየር ንብረት ለውጥ ድርድር አበጀህ የሚያስብሉትን ስኬቶች አስመዝግቧል፡፡ በቀዝቃዛው የዓለም ጦርነት ጊዜ አብዛኛው ሃገራት የገለልተኛ ሀገሮች ማህበር አባል ቢሆኑም የአፍሪካ ሀገሮች እርስ በእርሳቸው ተከፋፍለው አፍሪካን የጦርነት አውድማ አድርገዋት ነበር፡፡ አንዱ የአፍሪካ ሀገር የምዕራቡ ካምፕ ደጋፊ ከሆነ ሌላኛው የምስራቅ ካምፕ ደጋፊ ነበር፡፡ ሁለቱም ካምፖች ለርዕዮተ ዓለም ተከታዮቻቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ በማድረግ አፍሪካ እርስ በእርስ እንድትባላ አድርገዋል፡፡ ይህም ህብረቱ የተቀደሰ ሃሳብ ቢኖረውም የማስፈፀም አቅሙ ያን ያህል የተጠናከረ አለመሆኑን ያሳያል፡፡ ለህብረቱ የማስፈጸም አቅም ማነስ አንደኛው ምክንያት ከአባል ሀገራት የሚጠበቀውን ገንዘብ በአግባቡ አለመሰብሰቡ ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የህብረቱ የ2023 በጀት 654 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር እንዲሆን በዛምቢያ በተደረገ ጉባኤ ውሳኔ የተላለፈ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 60 በመቶ የሚልቀው በጀት ከለጋሾች እንደሚሰበሰብ በወቅቱ ይፋ ተደርጓል፡፡ በሌላ በኩል አፍሪካ በየዓመቱ 50 ቢሊዮን ዶላር በሙስና እንደምታጣ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ 1 በመቶ እንኳን ማዳን ቢቻል የህብረቱን የ2 ዓመት ወጪ መሸፈን ይቻላል ይላሉ ባለሙያዎች፡፡ ጥቂት በማይባሉ የህብረቱ አባል ሀገራት ሙስና ዛሬም አደጋ መሆኑ፣ የርስ በርስ ግጭት በሚፈለገው ደረጃ አለመፈታቱ፣ ድህነት አሁንም የአህጉሪቱ ቀንደኛ ጠላት መሆኑ፣ የትምህርትና ጤና አገልግሎቶች ተደራሽ አለመሆንና ጥራቱም የተጓደለ መሆን፣ በህብረቱ የሚወሰኑ ውሳኔዎች አፈጻጸም የተለያየና የሚፈለገውን ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ ውስንነት ያለበት መሆኑ ወዘተ የህብረቱና አባል ሀገራት ጉድለት ሆነው ቀጥለዋል። ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች የአፍሪካ ህብረት ከስኬቱም ሆነ ከልምዱ ለመማር የሚያስችለው ከግማሽ ክፍለ ዘመን የዘለቀ የእድሜ ባለፀጋ ሆኗል፡፡ እናም የወደፊት አቅጣጫውን ሲተልም ያለፈውን ጉዞ ዞር ብሎ ማየት፤ የቆመበትን ነባራዊ ሁኔታ ጠንቅቆ መረዳትና መጭውን አቅርቦ ማሰብ ይጠበቅበታል። ለዚህ ደግሞ የማስፈጸም አቅምን ማጠናከር፣ ለስራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት መስጠት፣ ተሳትፎን ማሳደግ፣ የገቢ አቅምን ማሳደግ ወሳኝ ናቸው። ሀ. የማስፈጸም አቅም የአፍረካ ህብረት ከአፍሪካ አንድነት ደርጅት የተሻለ አደረጃጀትና አሰራር እንዳለው የሚቀበሉ አሉ፡፡ ለምሳሌ በሀገሮች ጣልቃ ያለመግባት መርህን በማሻሻል ህብረቱ በመፈንቅለ መንግስት የመጡ ቡድኖችን በአባልነት አይቀበልም ነገር ግን በአፍሪካ አሁንም የእርስ በርስ ግጭት የሚታይባቸው ሀገሮች አሉ፡፡ ስለሆነም ይህንኑ ችግር ሊቀርፍ የሚችልና ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበ አደረጃጀትና አሰራር ሊኖረው ይገባል፡፡ የህብረቱ በጀት በሌሎች አካል መሸፈን አሉታዊ ተፅዕኖ ስለሚኖረው አባል ሃገራት የሚጠበቅባቸውን መዋጮ በወቅቱ በመክፈል የህብረቱን የማስፈፀም አቅም ማሳደግም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለ. የስራ እድል ፈጠራ የአፍሪካ ህብረት በተለይ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ማዕከል ያደረገ እድገትን ማበረታታት ግድ የሚለው ወቅት አሁን ነው፡፡ ሆኖም ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ከማረጋገጥ አኳያ ብዙ የሚቀሩ ስራዎች እንዳሉ እሙን ነው። በተለይም ወጣቶችን ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ መሰራት ያለባቸው የቤት ስራዎች በአግባቡ አለመሰራታቸው በጉልህ ይጠቀሳሉ፡፡ እንደ አፍሪካ ኢኮኖሚ አውትሉክ መረጃ በአፍሪካ እድሜያቸው ከ15 እስከ 25 ዓመት ያሉ ወጣቶች ከአህጉሪቱ አጠቃላይ ህዝብ ከ70 ከመቶ በላይ ይሸፍናሉ፡፡ የዓለም ባንክ ያወጣው መረጃ እንደሚያሳየው በአፍሪካ 200 ሚሊዮን የሚጠጉ እድሜአቸው ከ15 እስከ 25 የሚጠጋ ወጣቶች ሲኖሩ ከነዚህ መካከል 60 በመቶ የሚጠጉት ስራ ፈላጊ መሆናቸው ደግሞ ህብረቱ የሚጠብቀውን ከባድ ስራ ያሳያል፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በየሃገሮቹ ለወጣቶች ምን ያህል የስራ እድል እንደተፈጠረ መጠየቅን የእርስ በእርስ መገማገሚያ መድረኩ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ ሊያደርገው እንደሚገባ ምሁራን ይመክራሉ፡፡ ሐ. የህዝብ ተሳትፎና የውክልና ዴሞክራሲ ህብረቱ ሊያሳካ ያሰባቸውን ግቦች እውን ማድረግ የሚቻለው በሁሉም የነቃ ተሳትፎ መሆኑ አያጠያይቅም። በመሆኑም አባል አገራት ችግሮችን ከመለየት ጀምሮ እስከ ክትትልና ግምገማ ስርአት ህብረተሰቡን በሁለንተናዊ መርሃ ግብሮች ማሳተፍ ይገባቸዋል፡፡ ይህ ሲደረግ ነው በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ ያሉ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የፈጠራ ችሎታዎችን ማውጣትና ሀገሬ ለእኔ ምን አድርጋለች ሳይሆን እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ የሚሉ ዜጎችን መፍጠር የሚቻለው፡፡ በአፍሪካ በየቦታው የሚታዩ የእርስ በእርስ ግጭቶች መንስኤ በዋነኛነት የህዝብ ፍላጎት አለመሟላት ሲሆን በተለይም የአናሳዎች መብት አለመከበር የግጭት መንስኤ ሲሆን ይታያል፡፡ ለዚህ ደግሞ በየአካባቢው አስተዳደር ህዝቡን በየጊዜው ማማከር ያስፈልጋል፡፡ መ. ውስጣዊ የገቢ አቅምን ማሳደግ በዋናነት አራት የገቢ ምንጮች ያሉ ሲሆን እነሱም የሃገር ውስጥ ብድር፤ ግብርና ታክስ፣ የውጭ ብድር እና እርዳታ ናቸው፡፡ ከግብርና ታክስ በስተቀር ሌሎች የገቢ ምንጮች አሉታዊ ተጽዕኗቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ግብርና ታክስን በአግባቡ መሰብሰብ የአንድ ሀገር የሁለንተናዊ ብቃት መለኪያ ነው፡፡ ግብርና ታክስ የመንግስት ወጪ በመሸፈን ነጻነትን ከማጎናጸፉም በተጨማሪ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍልን ለማረጋገጥ ሁነኛ መሳሪያ ነው፡፡ አልጀዚራ ባወጣው መረጃ መሰረት አፍሪካ በእርዳታና በብድር ከምታገኘው ይልቅ በታክስ ማጭበርበርና ስወራ የምታጣው ከ10 እጥፍ በላይ ይበልጣል፡፡ ለዚህ ደግሞ የታክስ ህጎች ክፍተት መኖርና በሙስና የተጨማለቁ ባለስልጣናት እንዲሁም ብቃት ያለው የሰው ኃይል አለመኖር አስተዋፆኦ ያደርጋሉ፡፡ የገቢ አሰባሰብ ስርአቱን በማሻሻል የአፍሪካን ነጻነት ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአፍሪካን የእርስ በርስ ንግድ ማስፋፋት፤ የታሪፍና ቀረጥ ምጣኔን ማሻሻል፤ የወጪ ገበያ የምርት አይነቶችን ማስፋትና ሃገራቱን በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር የየሃገራቱን የተናጠል ጥረትና የህብረቱን አመራሮች የጋራ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራቱን በማስተባበር ባለፉት 60 ዓመታት ያለፈበትን የውጣ ውረድ ጉዞ በማጤን የተሻለ ነገን ለመገንባትና የአፍሪካን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከትላንቱ በበለጠ መትጋት ይገባዋል።      
"እንሰትና ሁለገብ ጠቀሜታው"
May 6, 2023 983
በፍሬዘር ጌታቸው እንሰት በኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ያስቆጠረ፤ በተለይ በደቡቡ የሀገሪቱ ክፍሎች በስፋት የሚመረት ተክል እንደሆነ የታሪክ ድርሳናትና በዘርፉ የተካሄዱ ጥናቶች ያስረዳሉ። እንሰት በደቡብ የሀገራችን ክፍል በሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝብች ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ነውና የምግብ ዋስትና አለኝታ ተደርጎ የሚወሰድ ተክል ነው። ተፍቆ ለምግብነት ወሳኝ የጤንነት መጠበቂያና የጥንካሬ መሰረት ተደርጎ ይወሰዳል። የእንሰት ተክል የሚጣል ነገር የለውም። ተረፈ ምርቱ ለእንሰሳት መኖ ጭምር ያለው ፋይዳ የላቀ ነው። እያንዳንዱ የእንሰት ተክል ክፍል ከምግብነት ባሻገር ለተለያዩ አገልግሎቶች ይውላል። የእንሰት ተክል ለም አፈር በንፋስና በጎርፍ ታጥቦ እንዳይወሰድ የመከላከል አቅሙ ከፍተኛ ነው። ከዚህም ባሻገር የአፈር ለምነትን እና እርጥበት ጠብቆ በማቆየት ለምርታማነት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው በመሆኑ ከደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች ሕዝቦች ጋር ያለውን ቁርኝት ዘመን ተሻጋሪ ያደርገዋል። ለአብነትም እንሰት በወላይታ ብሄር ከሰውና ከእንስሳት ምግብነት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን በአካባቢው "ኡታ" ተብሎ ይጠራል። እንሰት ወይም "ኡታ" የባለፀጋነት መገለጫም ነው። የመኖሪያ ቤቱን ዙሪያ፣ ቀዬውን በእንሰት የከለለና ያስዋበ፣ ማሳውን በእንሰት ያለማ አባወራ ባለጠጋ እንደሆነ ይታመናል። አባወራውም "አላ ኡታ ጎዳው" በማለት ይሞካሻል። እንሰት ለምግብነት፣ ለመደኃኒትነት፣ ለአካባቢ ውበት፣ ለአፈር እርጥበትና ለምነት ለመጠበቅ፣ ለእንሰሳት መኖነት፣ ለባህላዊ ቤት ስራ ጣራና ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት ያገለግላል። እንዲሁም ኮባው (ቅጠሉ) እንደ ዳቦ ለመሳሰሉት ምግብ ማብሰያና ለተለያዩ የግብርና ዉጤቶች መጠቅለያነት ግልጋሎት ይውላል። ከእንሰት ተረፈ ምርቶች የመቀመጫና የወለል ምንጣፎችን ጨምሮ በርካታ መገልገያዎች ይሰራሉ። የእንሰት ተክል በተለያዩ አካባቢያዊ ሁኔታ መብቀል ከመቻሉ ባሻገር ድርቅን የመቋቋም አቅሙ ከፍተኛ ነው። በዚህም አካባቢው ላይ ድርቅ በተከሰትበት ወቅት "ነፍስ አድን" የሚል ስያሜም ተሰጥቶት እንደነበር በታሪክ ይናገራል። የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር መለሰ መኮንን እንሰት ምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥና የልማት ችግሮችን ከማቃለል አንጻር ከፍተኛ ሚና ያለው ነው ይላሉ። ተክሉ በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብና በሲዳማ ክልሎች በስፋት እንደሚለማና በሀገሪቱ ከ3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በላይ በተለያየ የእንሰት ዝርያ መሸፈኑን ያስረዳሉ። ከሀገሪቱ ህዝቦች ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የእንሰት ተዋፅኦን የሚመገቡና የሚገለገሉ ናቸው። የእንሰት ተክል በባህሪው የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም የከፍተኛ አቅም ያለው በመሆኑ፤ ለዝናብ እጥረትና ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ተክሉን በስፋት በማልማት የምግብና ዋስትናን በዘላቂነት ማረጋገጥ ይቻላል ይላሉ። እንሰትን ለምግብነት ከመጠቀም ባሻገር ለገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ ሀብት በመሆኑ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የተሻለ አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ጥረት ማድረግ ይጠይቃል ሲሉ ያስረዳሉ ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር መለሰ። እንሰት በአካባቢው ማስገኘት ከሚገባው ጠቀሜታ አንፃር ሲታይ እየሰጠ ያለው ጥቅም ከአቅም በታች ነው የሚሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የእንሰት ሰብል ተመራማሪ ዶክተር አብርሃም ቦሻ ናቸው። በመሆኑም የእንሰትን ምርታማነት ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲው የምርምር፤ የማህበረሰብ አገልግሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን በትኩረት እየሰራ ነው ይላሉ። በኢትዮጵያ ከባህር ጠለል በላይ ከ1 ሺህ 500 እስከ 3 ሺህ 100 ሜትር ከፍታና አማካይ የዓመት ዝናብ መጠን ያለው አካባቢ ለእንሰት ተክል ምቹ ሲሆን፤ እንሰት ዝናብን የሚተካ አማራጭ የውሃ ምንጮች ባሉበት አካባቢ ከ1 ሺህ 500 ሜትር በታች በሆኑ ቆላማ አካባቢዎችም ምርት ሊያስገኝ ይችላል ይላሉ። እንደ ተመራማሪው ገለጻ እንሰት በሀገሪቱ ከሚገኙና ዋና ዋና ሰብሎች ከሚባሉት መካከል አንዱና ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው ነው። ተክሉ ተራራማ ቦታዎች ላይ ጭምር በምቾት የሚያድግ ሲሆን እንደ ዝርያው ዓይነት ከሶስት እስከ አምስት ዓመት ውስጥ ምርቱ ውጤታማ መሆን ይችላል። ዝርያው "ወንዴ" እና "ሴቴ" ተብሎ የሚከፈል ሲሆን፤ 60 ያህል የእንሰት ዝርያዎች አሉ። ከምርት አያያዝና ብቃት አንጻር ሲታይ ከእያንዳንዱ የእንሰት ተክል ከ40 ኪሎ በላይ ዱቄት ይገኝበታል። እንሰት ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ጉልህ አስተዋፅኦ ያለው ሰብል ነው፤ ከዛም አልፎ ለሰውና ለእንስሳት ከተለያየ በሽታ የመከላከልና ከጉዳት ለማገገም የሚያስችል መድኃኒት ነው። ተክሉን የማባዛት ስራ በባህላዊ መንገድ የሚከወን ሲሆን፤ የእንስሳትና ሌሎች የሚወገዱ ተረፈ ምርቶችን በመጨመር እድገቱን ውጤታማ ማድረግ ይቻላል። ከእንሰት ምርት የሚገኘው ዱቄት ቡላ ወይም በአካባቢው አጠራር "ኢቲማ" ለልጆችና ለአዋቂዎች ጤና ተስማሚ ሲሆን፣ ገንፎ፤ የክትፎ የአይብና ጎመን ማባያ ቆጮ "ኡንጫ" እንዲሁም ሙቾና ባጭራ ለምግብነት ከሚውሉት ተጠቃሽ ናቸው። የእንሰት ተክል በተለያዩ የአፈር ዓይነቶች ላይ የሚለማ፣ የአየር ንብረት ለውጡን የመቋቋም አቅም ያለው ተክል ነው። የወላይታ ዞን እንሰት አብቃይ ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ ሲሆን በተለይም በባይራ ኮይሻ፣ በቦሎሶ ሶሬና በአንዳንድ የሶዶ ዙሪያ ወረዳዎች በተደረገ የዳሰሳ ጥናት የእንሰት ተክል የመመናመንና የበሽታ አደጋ እንደተጋረጠበት ዶክተር አብርሃም አብራርተዋል። ለዚህም ምርቱን መልሶ ለማስፋፋትና ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ከዞኑ ግብርና መምሪያ ጋር በመሆን በትብብር እየተሰራ መሆኑን ያስረዳሉ። የወላይታ ዞን የግብርና መምሪያ እርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ዓለሙ እንዳሉት በወላይታ ዞን ከ28 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በእንሰት ተክል የተሸፈነ ነው። የእንሰት ተክል የሚፈለገውን ምርትና ውጤት እንዳይሰጥ ከሚያደርጉ ተግዳሮቶች መካከል ዋነኞቹ የአጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ፣ የተለያዩ ተባዮች፣ ፍልፈልና ጃርት ይጠቀሳሉ። የእንሰት አጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ በሁሉም የእንሰት አብቃይ ስነ-ምህዳር የሚገኝ፣ በሁሉም የእድገት ደረጃ ላይ ያለን የእንሰት የሚያጠቃና ከአንዱ ወደ ሌላው ተክል የሚተላለፍ መሆኑ ችግሩን የከፋ ያደርገዋል። በመሆኑም ችግሩን ለማስወገድ ጤነኛ የእንሰት ተክሎችን በላቦራቶሪ የማባዛት፣ የበሽታ አምጪ ተህዋሲያን የማጥናትና በጄኔትክ ምህንድስና በሽታን የሚቋቋም ቅንጣት ወደ እንሰት የማስገባት ሥራ እየተሰራ ነው። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣ ከሶዶ ግብርና ኮሌጅ እንዲሁም ከአረካ የምርምር ማዕከል ጋር በመሆን በጋራ እየተሰራ ነው። ኃላፊው እንዳስረዱት ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በሽታን የሚቋቋሙ ከ20 ሚሊዮን በላይ የእንሰት ችግኞችን አባዝቶ በመትከል የተሻለ ውጤት እየታየ ነው። ይህን ሥራ በማጠናከር ከእንሰት ዘርፍ ሊገኝ የሚገባውን ጥቅም ለማግኘት አርሶ አደሩ ያለውን አገር በቀል ዕውቀቱን በአግባቡ እንዲጠቀም በከፍተኛ ንቅናቄ እየተሰራ ይገኛል። በዚህም የአካባቢውን የእንሰት ሽፋን ማሳደግ ብቻ ሳይሆን የአርሶ አደሩን ጥያቄ መመለስና ጥቅሙን ለማላቅ የተጀመረው የንቅናቄ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ወሳኙ ስራ ተደርጎ እየተከናወነ ነው። ማህበረሰቡ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የአየር ንብረት ፋይናንስ-አፍሪካውያን ገፍተው ያልሄዱበት መንገድ
Feb 18, 2023 1571
/በገዛኸኝ ደገፉ/ የአፍሪካ ቀንድ ከ40 ዓመታት ወዲህ ተከስቶ አያቅም የተባለለትን የድርቅ አደጋ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ ሆነዋል። የድርቁ አደጋ የከፋበት የአፍሪካ ቀንድ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ተሸክመዋል። በተጨማሪም የከተሞች መስፋፋትና የከተሜነት የኑሮ ዘይቤን እያስተናገደች ባለችው አፍሪካ የኃይል እጥረት፣ በቂ የመሰረተ ልማት አውታሮች ዝርጋታ አለመኖር፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት፣ ሥራ አጥነት ብሎም የወንጀሎች መስፋፋት አሕጉሪቱን ክፉኛ እየፈተኗት ይገኛሉ። የገጠር መሬት ምርታማነት መቀነስ ከገጠር ወደ ከተማ ለሚደረገው ፍልሰት አንደኛው ገፊ ምክንያት ሲሆን ለመሬቱ ምርታማነት መቀነስ ሰበብ ተደርጎ በዋናነት የሚጠቀሰው ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት የሚወልዳቸው የውኃ ኃብት መቀነስና ለተከታታይ ዓመታት የሚዘልቁት የድርቅ አደጋዎች መሆናቸው ጉዳዩን ይበልጥ አወሳስቦታል። እንደ አህጉር ከ4 በመቶ ያነሰ የካርቦን ልቀት ያላት አፍሪካ 65 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ መሆን ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። ከዚህ ችግር ሙሉ ለሙሉ መውጣት ባይቻልም ትርጉም ባለው ደረጃ መቀነስ እንዲቻል አህጉሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ኃብትና ወጣት የሰው ኃይል በማስተሳሰር ለውጥ ማምጣት ግድ ይላታል። በአፍሪካ የማይቀረውን የከተሞች መስፋፋትም ሆነ የህዝቦቿን የመልማትና የመለውጥ ፍላጎት ማሟላት ካለባት የአየር ንብረት ፋይናንስን የበለፀጉ ሀገራት ገቢራዊ ሊያደርጉት ይገባል። የአየር ንብረት ፋይናንስ (Climate Finance) የአካባቢ፣ ብሔራዊ ወይም ድንበር ተሻጋሪ ፋይናንስን የሚመለከት ሲሆን ከሕዝብ፣ ከግል እና ከአማራጭ የገንዘብ ምንጮች የተውጣጣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለማስተካከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ስምምነት ነው። የኪዮቶ ፕሮቶኮል እና የፓሪስ ስምምነት ደግሞ ሰፊ የገንዘብ አቅም ካላቸው አገራት አነስተኛ የኃብት አቅም ላላቸው እና ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ አገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ስምምነት ነው። ስምምነቱ “የጋራ ግን ደግሞ ልዩነት ያለው ኃላፊነትና አቅም” በሚለው መርህ መሰረት ያደጉ አገሮች አዳጊ አገራትን ለመርዳት የገንዘብ ምንጮችን እንዲያቀርቡ ይጠይቃል። ፋይናንሱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ወሳኝ ድጋፍ እንደሚሆን ታምኖበታል። ምክንያቱም ልቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ላቅ ያለ የኢንቨስትመንት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ። በተመሳሳይ ከአሉታዊ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎች ጋር ለመላመድ እና ተለዋዋጭ ጫናዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ይጠይቃል። ከጥቂት አሥርት ዓመታት በፊት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበው የምእተ ዓመቱ የልማት ግብ ሰነድም ሆነ በቅርቡ በሚጠናቀቀው ዘላቂ የልማት ግቦች ላይ ለጉዳዩ ከፍ ያለ ትኩረት ቢሰጠውም እስካሁን ግን የፈየደው ነገር የለም። አፍሪካ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችን ለመላመድ ዓመታዊ 41 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የፋይናንስ ክፍተት ይገጥማታል። ይህን ክፍተት ለመሙላት አዲስ አበባ እያስተናገደች ባለችው 36ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ የአየር ንብረት ፋይናንስ ገቢራዊ ማድረግን ቀዳሚ ትኩረታቸው መሆን እንዳለበት የአንድ ዘመቻ (ONE Campaign) አጽንኦት ሰጥቶ ምክረ ሃሳቡን ሰንዝሯል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የአንድ ዘመቻ ዳይሬክተር ዶሪን ኒኒናሃዝዌ የአፍሪካ መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመላመድ ፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥን አስከፊ ተጽዕኖ የመቋቋም አቅም እንዲገነቡ መክረዋል። አፍሪካ ባልፈጠረችው የአየር ንብረት ለውጥ ህዝቦቿ ለከፋ ጥቃት እየተዳረጉ ይገኛሉ። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች የበለጸጉ አገሮች የገቡትን የማላመድ ፋይናንስ ድጋፍ ቃል እንዲፈጽሙ ከማግባባት ባለፈ ማሳሰብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይህ ማለት እኤአ ከ2020 እስከ 2025 በዓመት 100 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመተውን ግብ የማሳካት ተግባር የሚጠይቅ ነው። ከዚህ ባሻገር በቀጣዮቹ ዓመታት በተጨመሩ መዋጮዎች የሚስተዋሉ ጉድለቶችን መፍታት እና በግብጿ ሻርም ኤል ሼክ ከተማ ባስተናገደችው COP-27 ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ለመላመድ በእጥፍ ፋይናንስን የማቅረብ ቁርጠኝነት የማቅረቢያ ዕቅድ ሊነድፉ ይገባል ነው ያሉት። የአፍሪካ አገሮች ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ከሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ጋር ሲታገሉ ቢቆዩም አሁን ላይ “አፍሪካ በአፈፃጸሙ ላይ መጠነኛ መሻሻል አሳይታለች” ብለዋል። እናም በ36ኛው የመሪዎቹ ጉባዔ የተገኙ ስኬቶች እና የጠፉ ዕድሎች እንዲሁም የድርጅቱን ዓላማዎች ለማሳካት በአየር ንብረት ፋይናንስ በጥልቀት መክረው ለተሻለ ስኬት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዋና ዳይሬክተር አንቶኒዮ ቪቶሪኖ በአየር ንብረት ምክንያት የሚፈጠሩ መፈናቀልን ለመግታት የተሻሻሉ የመላመድ እና የተጽዕኖ ቅነሳ ተነሳሽነት ገቢራዊ ለማድረግ በአገራት መካከል ጠንካራ አጋርነትን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ያሰምሩበታል። በተለይ በአፍሪካ ቀንድ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ኑሯቸውን መሰረት ባደረጉ ህዝቦች ላይ አውደ-ተኮር መላመድ እና የመቋቋም አቅም ግንባታ መፍጠር ይገባል። ለዚህ ደግሞ መላመድን የሚደግፉ ፋይናንስ ለማግኘት የሚረዱ መመሪያዎች ይበልጥ የተፍታቱ መሆን ይኖርባቸዋል ሲሉ ቪቶሪኖ ይሞግታሉ። ከ 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በተጓዳኝ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ (High-Level Forum) ላይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በሻርም ኤል ሼክ በተካሄደው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መላመድን፣ መከላከልን እና ዝግጁነትን ለማሻሻል ዓለም አቀፍ ትብብር ማጎልበት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አውስተዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥን አስመልክቶ ያወጣቸው የስምምነት ማዕቀፎች (United Nations Framework Convention on Climate Change (UNFCCC)) በርካታ ዝርዝርና ሚዛናዊ አካሄዶችን የያዙ ናቸው። ያም ሆኖ አተገባበራቸው እዚህ ግባ የማይባል በመሆኑ የሚታሰበውን ያህል ለውጥ ማምጣት ሳይችል ቀርቷል። በዚህም ቦረና ዞንን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የአየር ንብረት መዛባት፣ የሙቀትና የባህር ጠለል መጨመር፣ ጎርፍ፣ ድርቅ እንዲሁም ያልተገመቱ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ዓይነተኛ አማራጭ እንደሆነ ብዙዎቹ ይስማሙበታል። ዳሩ ግን አገራትን፣ አህጉርን፣ ዓለምን እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ግዙፍ ኩባንያዎችን ያስተሳስራል የተባለለት የአየር ንብረት ፋይናንስ በቅጡ ገቢራዊ ማድረግ ባለመቻሉ የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በርካታ ህዝቦች ዳፋውን ለመጋፈጥ ተገደዋል። የአየር ንብረት ፋይናንስን በመተግበር በመስኩ የተጎጂዎችን ቁጥር ሊቀንሱና የዓለምን ሥነ-ምህዳር ከተቻለ ወደ ቀድሞው ሊመልሱ አሊያም አሁን ባለበት አረጋግተው ሊያቆዩ የሚያስችሉ በርካታ አማራጮች ተግባራዊ ሊደረጉ ይገባል። ለአብነትም ለድሃ ሃገራት አርሶ አደሮች የግብርና ምርቶች ተገቢውን ዋጋ በመክፈል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን እንዲቋቋሙ ማድረግ ከአማራጮቹ መካከል አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግዙፎቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሚያስወግዷቸው በካይ ጋዞች ተመጣጣኝ የጤና ሥርዓት በመዘርጋት የታዳጊ ሃገራት ዜጎችን የጤና አገልግሎት ማሻሻል ሌላው አማራጭ ነው። የተፈጥሮ ኃብቶችን የሚጎዱ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ተፈጥሮን በሚንከባከቡ ዘዴዎች መተካት እንዲሁም ብክለትን የሚያስቀሩ የምርት ሂደቶች መለማመድ ጥቂቶቹ የመፍትሄ አማራጮች ተደረገው የሚወሰዱ ናቸው። በፓሪስ ከተደረሰውን የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ቀደም ብሎ በፈረንጆቹ 1994 ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም (Global Environment Facility-GEF) COP-16 ዓለም አቀፍ ጉባዔ በኋላ በ2010 አረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ (Green Climate Fund-GCF) እንዲሁም በ2001 ደግሞ ልዩ የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ (Special Climate Change Fund-SCCF) እና የመላመድ ፈንድ (Adaptation Fund-AF) የተባሉ ማዕቀፎች የተዘጋጁ ቢሆንም ስለጉዳዩ የሚያስረዱ ተከታታይ ስብሰባዎች ከማዘጋጀት በዘለለ ብዙ ርቀት መጓዝ ሳይችሉ ቀርተዋል። በቅርቡ በአለም ባንክ አሰባሳቢነት በኬንያ ናይሮቢ ተዘጋጅቶ በነበረው የአህጉሪቱን መሪዎች ባለሃብቶችንና ምሁራንን ባካተተውና “One Planet Summit” በተሰኘ መሰል ጉባዔ ላይም አፍሪካውያን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚገጥማቸውን ችግሮች ተከላክለው ሁለንተናዊ ዕድገታቸውን እንዲያፋጥኑ ካስፈለገ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምጣኔ ኃብት ፖሊሲ አዘጋጅተው መተግበር እንደሚኖርባቸው መግባባት ላይ የተደረሰ ቢሆንም አሁንም ጥያቄ ያስነሳው አፈጻጸሙ ስለመሆኑ ብዙ ተብሎለታል። ክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ የተባለ ድርጅት ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያመለክተው አፍሪካ እንደ ፈረንጆቹ የጊዜ ቀመር ከ 2020 እስከ 2030 ባሉት አሥር ዓመታት 2 ነጥብ 8 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር አሊያም በየዓመቱ ከ2 መቶ ሃምሳ ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያስፈልጋት ሲሆን አህጉሪቱ ከዘርፉ እያገኘችው ያለው ገንዘብም ከሚያስፈልጋት 12 በመቶውን ወይም 30 ቢሊየን ዶላር ብቻ ስለመሆኑ አስነብቧል። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው ሊሰሩ የሚችሉ በርካታ ተግባራት እንዳሏት የሚያትተው ሪፖርቱ ከአየር ንብረት ፋይናንስ የሚገኘው ገንዘብ በትራንስፖርት፣ በኃይል ልማት፣ በኢንዱስትሪ ብሎም በግብርና፣ በአፈርና በደን ኃብት አጠቃቀም ውጤታማ በሆነ መንገድ ከዋለ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ኃብቶች መንከባከብ ከማስቻሉም ባለፈ ላቅ ያለ ፋይዳ ይኖራዋል ብሏል። ይህ ሲሆን የሥራ ዕድል በመፍጠር የሥራ አጥ ቁጥርን በመቀነስ ለአህጉሪቱ ሰላምና መረጋጋት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖው ያስረዳል። ላለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ገቢራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራን የማስፋፋትና የተጎዱ አካባቢዎችን የማከም ሥራ እንዲሁም አይቀሬ የሆኑትን ከተሜነትና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ታሳቢ ያደረጉ የአየር ንብረት ፖሊሲዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ለአፍሪካ ሃገራት እየፈጠረው ያለው በጎ ተጽዕኖ በግልጽ እየታየ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ጥረት ግን በአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲደገፍ አገራዊና የተቀናጀ አሕጉራዊ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል። ከአጠቃላይ የአፍሪካ አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ግብጽ ብቻ 151 ቢሊየን ዶላር ከአየር ንብረት ንብረት ፋይናንስ ማግኘት እንደሚኖርባቸው የክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ ሪፖርቱ ይገልጻል። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በመጭው የCOP-28 ጉባዔ የራሷንና የአፍሪካን ፍላጎት የሚያስጠብቁ የፋይናንስ ትልሞችን የመንደፍ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባታል፡፡ የ COP-27 ጉባዔ ለአፍሪካ ያስገኘውን ውጤት እና አንድምታ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የመሪዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ እና አስተባባሪ በሆኑት በኬንያው ፕሬዝዳንት ሰብሳቢነት በኅብረቱ የአዲስ አበባ ጉባዔ ላይ በጥልቀት ይገመግማል ተብሎ ይጠበቃል። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ ጥረቷን የሚያጎለብት የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ጠንካራ ተሳትፎ ልታደርግ ይገባል። የአፍሪካ አገራት ገፍተው ረጅም ርቀት ያልሄዱበት የአየር ንብረት ፋይናንስ እና ሌሎች የድጋፍ አማራጮችን በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት በመጠቀም የአየር ንብረት ተጽዕኖን የሚቋቋሙበት ጠንካራ አቅም ሊገነቡ ግድ ይላቸዋል። በእርግጥም አፍሪካውያን መሪዎች በሚያደርጉዋቸው ስብሰባዎች በየማዕዝናቱ በድርቅ ሳቢያ ለምግብ እጦት የተዳረጉ ህዝቦቻቸውን የሚታደጉበት ሁነኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበትን ዘዴ ነድፈው ረጅም ርቀት ሊጓዙ ይገባል። ”
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 3044
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 1727
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 2795
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 1807
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል።   “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል።   ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 1959
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
በብዛት የታዩ
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 4092
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 3720
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 3575
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 3044
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
በብዛት የታዩ
ስፖርታዊ ውድድሮችን ለቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
Feb 26, 2023 4092
ሀዋሳ (ኢዜአ) የካቲት 19/2015 በኢትዮጵያ ከተሞች ስፖርታዊ ውድድሮችን በማስፋፋት ለቱሪዝም ዕድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወት እየተሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶችን ጨምሮ 3 ሺህ 500 ሰዎች የተሳተፉበት 11ኛው የሶፊ ማልት ግማሽ ማራቶን ውድድር ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። በውድድሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳስታወቁት፤ የተለያዩ ኩነቶችን በማዘጋጀት ቱሪዝምን ለማነቃቃትና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ከአዲስ አበባ ውጭ በሀዋሳና በቆጂ ስፖርታዊ ውድድር ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰው፤ በሌሎች የክልል ከተሞች መሰል ውድድሮችን በማስፋፋት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከተማዋ ለስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ትላልቅ ኩነቶች ምቹ በመሆኗ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተስተናገደባትና ቱሪዝሙም እየተነቃቃ እንደሆነ ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሩ ለከተማዋ የቱሪስት ፍሰት ጉልህ አስተዋጽኦ ከማበርከቱም ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እያገዘ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በየዘርፉ ያሉ ስፖርተኞችን ለሀገር በማበርከት የምትታወቀው ሀዋሳ አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ለማፍራት የምትሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅ ዳግማዊት አማረ ውድድሩን ስናዘጋጅ በዋናነት የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የትኩረት ማዕከል በማድረግ ነው ብለዋል። ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር በጋራ እየሰራን ነው ያሉት አዘጋጇ፤ ከተሳታፊዎች መካከል እጣ የደረሳቸው በኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን ገልጸዋል። በውድድሩ ከግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የስምንት ኪሎ ሜትር እንዲሁም የህፃናትና አዋቂዎች ውድድር መካሄዱን ጠቁመዋል። በ21 ኪሎ ሜትር ውድድር በወንዶች አንድ ሰዓት ከአንድ ደቂቃ 52 ሴኮንድ በሆነ ጊዜ አንደኛ የወጣው አትሌት አበባው ደሴ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት ውድድሩ ብርቱ ፉክክር የታየበት መሆኑን ተናግሯል። የሀዋሳ አየር ንብረት ፀባይ ለውድድሩ ምቹ እንደሆነ ጠቅሶ በከተማዋ ተመሳሳይ ውድድሮች ሊስፋፉ እንሚገባ ጠቁሟል። በሴቶች አንድ ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ አንደኛ የወጣችው አትሌት የኔነሽ ደጀኔ ውድድሩ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ተናግራለች። እንዲህ አይነት ኩነት ለተተኪ አትሌቶች መፍለቅ የሚያበረክተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎች ከተሞችም ተጠናክሮ ቢቀጥል መልካም እንደሆነ አመልክታለች። በውድድሩበ አንደኝነት ላጠናቀቁ ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር እንዲሁም በወንዶች ከአንድ ሰዓት በፊት በሴቶች ደግሞ ከ70 ደቂቃ በፊት ውድድሩን ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ተጨማሪ ሽልማት ተዘጋጅቶ እንደነበርም ተጠቁሟል።
ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት
Mar 8, 2022 3720
የካቲት 29/2014 (ኢዜአ) ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ላይ የሚገኙ ሴቶችን በዘላቂነት በማቋቋም መሆን አለበት ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡በዓለም ለ111ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ እለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የተለያዩ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የሴቶች አደረጃጀቶች ተቀናጅተው የሴቶችን መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሰሩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት በተለይ ሴቶች ይበልጥ ተጎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። በርካታ ሴቶች ለጾታዊና አከላዊ ጥቃት መዳረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ስናከብር በችግር ውስጥ የሚገኙ እናትና እህቶቻችንን በዘላቂነት ለማቋቋም ድጋፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል ነው ያሉት። ከየካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ማድረግን ዓላማ ያደረገ አገር አቀፍ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚተገበር እቅድ በማውጣት ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን እየደገፉ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡ የአንድ ማዕከል አገልግሎትና የተሃድሶ ስራዎች ደግሞ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በዚህም ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በቀላሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 3575
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
ዛሬ የሚጀመረው 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል
Feb 18, 2023 3044
"የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መቀላጠፍ" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2019 ወደ ሥራ የገባውንና 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ሕዝብ በንግድ ለማስተሳሰር የታለመውን የንግድ ቀጣና ይበልጥ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራል። በተለይም ደግሞ የጋራ የጉምሩክ ሥርዓትና ወጥ የታሪፍ አስተዳደር በአህጉሪቷ ለመተግበር ትኩረት ይደረግበታል ተብሏል። ሌሎችም የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነትን የሚያቀጭጩ አሰራሮች ነቅሶ በማውጣት የተሳለጠ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር ምክክር አድርገው አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። የአፍሪካ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ በአፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ እንዲሁም በዩክሬንና በሩስያ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀው የአህጉሪቱ የምግብ ዋስትና ችግር እልባት በሚሰጡ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሏል። በተለይም ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የግብርና ሥራ ለማሳለጥና በአህጉሪቱ ዘመናዊ የእርሻ ሥራ በሚስፋፋባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። ይህም በዘላቂነት የአህጉሪቱን የምግብ ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ተብሏል። በመሆኑም የዛሬው ጉባዔ ትኩረቱ በዚሁ የምግብ ዋስትና ሁኔታ ላይ እንደሚሆን ብዙ ግምት ተሰጥቶታል። የአፍሪካ የ2063 አጀንዳ አፈጻጸም ባለፉት አሥር ዓመታት በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት የተጣለውን የረዥም ጊዜ ዕቅድ ከግምት በማስገባት የተሰሩ ሥራዎች ይገመግማል ተብሏል። ለቀጣይ አሥር ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚችሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጎ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ነው የተገለጸው። በተለይም ደግሞ ዋና ዋና የሚባሉ ስኬቶችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መጪውን አሥር ዓመት የተሻለ ለመፈጸም የሚያስችል የትግበራ ማዕቀፍ እንደሚዘጋጅ ይጠበቃል። ከዚህም ባሻገር አፍሪካ በፋይናንስ ራሷን እንድትችል እየተደረገ ያለውን ጥረትም ትልቅ ሥፍራ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል። ለአብነትም የኅብረቱ ሰላም ፈንድ የሚደረገው የአባል አገራት መዋጮና አገራት ከታክስ ገቢያቸው ለኅብረቱ በማዋጣት አጠቃላይ የኅብረቱን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገውም ጉዳይ ምክክር ሊደረግበት የሚችል ጉዳይ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በቻድ፣ በካሜሮን፣ ኒጀር፣ በናይጄሪያ አካባቢው ከጽንፈኝነት ጋር በተያያዘ በርካታ የጸጥታ ችግሮች እየተከሰቱ ሲሆን ይህም ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍልም የትጥቅ ትግል መቀስቀሱ የተዘገበ ሲሆን ይህም አገሪቱን ከሚያዋስኑ አገራት ጋርም አለመረጋጋት ፈጥሯል። በሰሜን ሞዛምቢክ ያለው የጸጥታ ችግርም አሁንም እልባት ያላገኘ ጉዳይ ነው። ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ትግበራ ሂደት ላይ ናቸው፤ ሱዳን ሕዝባዊ አስተዳደር ለመመሥረት የሽግግር ትግበራ ላይ ናት። በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በእነዚህና በሌሎች የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ምክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
የአገሪቷ ዓለም አቀፍ ውክልና እንዲጎላ እየተሰራ ነው-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
May 17, 2018 2876
አዲስ አበባ ግንቦት 9/2010 ኢትዮጵያ አሁን በዓለም ካላት የፖለቲካና ዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ እንዲሁም ተሰሚነትና ተደማጭነት ረገድ ያላትን ውክልና ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥቷል። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ መለሰ ዓለም በዚሁ ወቅት እንደተናሩት በሁለተኛው እድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ እንዲከፈቱ ከተያዙ ሚሲዮኖች መካከል በሞሮኮ፣ በአልጄርያና በሩዋንዳ ኤምባሲዎችን፤ እንዲሁም በቱሪክ ኢስታምቡል ቆንስላ ጄነራል መክፈት ተችሏል። በቀጣይ  በርካታ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችን በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በእስያና ኦሺኒያ እንዲሁም በመካክለኛው ምስራቅ አገራት ለመክፈት መታቀዱንም ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል። ይህም ውክልናን ለማስፋት፣ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ለማሳደግ፣ የዜጎችን መብት ለማስከበር፣ የኢንቨስትመንት፣ የቱሪዝም፣ የገጽታ ግንባታ እንዲሁም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማፋጠን ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ነው የጠቀሱት፡፡ በኢህአዴግ በኩል የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችም ለአገሪቱ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መዳበር የጎላ ሚና እንደሚኖራቸው አቶ መለሰ አብራርተዋል። የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ወገኖች በቅርቡ በአዲስ አበባ የተፈራረሙት የሰላም ስምምነት ማሳለጫ መድረክ እንዲተገበር ኢጋድና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግፊቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በመግለጫው ተጠቁሟል። ለሰላም ስምምነቱ መተግበር በዋና ዋና ተቀናቃኞች በኩል ቁርጠኝነት መኖሩን የገለጹት አቶ መለስ አንዳንድ ቦታዎች የሚታዩ ውጥረቶች ተፈተው ተግባራዊነቱ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 2795
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ
Feb 12, 2023 2655
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 5/2015 በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸናፊ ሆነዋል። ዛሬ ማለዳ በተደረገው ውድድር በወንዶች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1 እስከ 10 እንዲሁም በሴቶች ከ1 እስከ 8 በመውጣት ፍጹም የበላይነትን ይዘዋል። በወንዶች አትሌት አብዲሳ ቶላ 2 ሰዓት ከ5 ደቂቃ ከ42 ሴኮንድ ውድድሩን በመጨረስ አሸንፏል። አትሌት አብዲሳ በአሜሪካ ኦሬጎን በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በተካሄደው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በወንዶች ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ ታናሽ ወንድም ነው። አትሌት ደሬሳ ገለታ እና አትሌት ሃይማኖት አለው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ይዘዋል። በሴቶች አትሌት ደራ ዲዳ 2 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ11 ሴኮንድ በመግባት የውድድሩ አሸናፊ ሆናለች። አትሌት ደራ የአትሌት ታምራት ቶላ ባለቤት ነች።አትሌት ሩቲ አጋ እና አትሌት ስራነሽ ይርጋ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል። በሁለቱም ጾታዎች ያሸነፉት አትሌቶች በተመሳሳይ የ80 ሺህ ዶላር ሽልማት ያገኛሉ። በተያያዘ ዜና ዛሬ ማለዳ በተካሄደው የሆንግ ኮንግ ማራቶን በሴቶች አትሌት ፋንቱ ኢቲቻ 2 ሰዓት ከ27 ደቂቃ ከ51 ሴኮንድ በመግባት አሸንፋለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ አትሌት ስንቄ ደሴ ሁለተኛ ወጥታለች።በወንዶች ኬንያዊው አትሌት ፊልሞን ኪፕቶ ኪፕቹምባ አሸንፏል። ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች ልመንህ ጌታቸው እና ሰንበታ ገዛ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።
በድሬዳዋ በዕቅድ ዘመኑ ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተጠቆመ
May 24, 2018 2434
ድሬዳዋ ግንቦት 16/2010 በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዓመታት በተከናወኑ ተግባራት የገጠሩ ሕብረተሰብ በኢኮኖሚና በማህበራዊ አገልግሎቶች  ተጠቃሚ ቢሆንም ወጣቶችን የሥራ ዕድል ባለቤት ከማድረግ አንጻር ውስንነት መኖሩን የድሬዳዋ አስተዳደር ገጠር ነዋሪዎች ተናገሩ። በዕቅዱ የሁለት ዓመት ተኩል አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ  ውይይት ሲደረግ ነዋሪዎቹ እንዳሉት ለወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል የጎላ ክፍተት በመኖሩ የተቀናጀ ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል። በአስተዳደሩ የዋሂል የገጠር ቀበሌ ነዋሪ አቶ አህመድ መሀመድ እንዳሉት ባለፉት ሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ የገጠሩ ሕብረተሰብ በአካባቢው የትምህርት፣ የጤናና የመንገድ አገልግሎት በማግኘቱ ተጠቃሚ ሆኗል። የመስኖ ልማት ተደራሽነት እያደገ በመሆኑም በአካባቢያቸው የተወሰኑ ሰዎች የልማቱ ተጠቃሚ በመሆን ገቢያቸውን በማሳደግ ላይ መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡ በአሁኑ ወቅትም የመንገድ ውስኑነት መኖሩን የገለጹት አቶ አህመድ፣ በአካባቢው ለወጣቱ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግሮችን ለመፍታት ተገቢ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ ጠይቀዋል። የለገኦዳ ገጠር ቀበሌ ነዋሪ አቶ መሐመድ አብዱላሂ በዕቅድ ዘመኑ የገጠሩን ሕብረተሰብ ለመለወጥ የተደረገው ጥረት አበረታች ቢሆንም በሪፖርት የቀረበውና በተጨባጭ መሬት ላይ የተሰራው አንደማይጣጣም ጠቁመዋል። ወጣት ዚያድ አደም በበኩሉ "ባለፉት ሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ የገጠሩን ወጣቶች የሥራ ዕድልና የተዘዋዋሪ ገንዘብ ብድር አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ የተደረጉ ጥረቶች በገጠር ካለው የሥራ አጥ ወጣቶች ቁጥር ብዛት አንጻር አነስተኛ ነው" ብሏል፡፡ ተደራጅተውና ሰልጥነው ወደሥራ ለመሰማራት በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙት በርካታ ወጣቶች ተገቢ ድጋፍ በማድረግ  ጥያቄዎቻቸውን በአግባቡ መመለስ እንደሚገባ አመልክቷል፡፡ በተመሳሳይ ዜና በሁለተኛው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የሁለት ዓመት አፈጻጸም ላይ የድሬደዋ ከተማ ሴቶችና ወጣቶች ተወያይተዋል። በእዚህ ወቅት ተሳታፊዎች እንደተናገሩት ለከተማ ሴቶችና ወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት የተከናወኑ ተግባራት አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል። ከተሳታፊዎቹ መካከል ወጣት አዲስ ዘመድሁን እንዳለው አምናና ዘንድሮ ለወጣቱ ብድርና ስልጠና በመስጠት ወደሥራ እንዲገባ መንግስት ያከናወናቸው ተግባራት በወጣቱ ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል፡፡ ይሁንና የገበያ ትስስር የመፍጠር፣ የመስሪያና የመሸጫ ቦታዎች የማመቻቸት ክፍተቶች ቢስተካከሉ በዕቅዱ የተቀመጡ ግቦችን በተሻለ ማሳካት እንደሚቻል አመልክቷል፡፡ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚደረጉ ድጋፎች የተሻሉ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ ወይዘሮ ከዲጃ አሊ የተባሉ የድሬደዋ ከተማ ነዋሪ ናቸው፡፡ "የሴቶች ማህበራዊ፣ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳካት ከተፈለገ መንግስት የሚያወጣቸው ዕቅዶችና መመሪያዎች በአግባቡ ያለመተግበር ክፍተቶችን ማረም ይገባል" ብለዋል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደርን የሁለተኛ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈጻጻም ሪፖርት ያቀረቡት የድሬዳዋ ፕላንና ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ ተሰማ ባለፉት ሁለት ዓመታት በአስተዳደሩ የግብርናው ዘርፍ  በ4 ነጥብ 5 በመቶ ማደጉን ገልጸዋል። በገጠርና በከተማ በመንገድ፣ በትምህርትና በጤና መስክ የተቀመጡትን ግቦች ለማሳካት የተከናወኑ ተግባራት በጥሩ አፈጻጻም ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል፡፡ የሴቶችንና የወጣቶችን ተሳተፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሥራዎች ቢሰሩም ከሚጠበቀው ግብ አንጻር በቂ ባለመሆኑ በቀጣይ የተቀናጀ ሥራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በአስተዳደሩ የሥራ አ ጥ ምጣኔ በ2007 ከነበረበት 32 በመቶ ወደ 15 ዝቅ ቢልም ከተቀመጠው 12 በመቶ አንጻር ሲታይ ተጨማሪ ጥረቶችን ማድረግ አሰፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በውይይት መደረኮቹ ላይ የተገኙት የኢፌድሪ የመገናኛና ኢንፎርሜሽንና ቴክሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሲሳይ ቶላ በበኩላቸው በመላው አገሪቱ በየደረጃው ከሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በዕቅዱ አፈጻጸም ላይ ውይይት እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። በውይይቱ ላይ ከሕብረተሰቡ የሚነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተቀምረው በቀጣይ ሁለት ዓመት ተኩል ዕቅዱን በተሻለ ለማስፈጸም ርብርብ ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ አቶ ሲሳይ እንዳሉት በዕቅዱ የሁለት ዓመት ተኩል አፈጻጸም በትምህርት፣ በጤና፣ በመሰረተ ልማት ዘርፎች ውጤታማ ሥራዎች ተሰርተዋል። በቀጣይ ቀሪ ዘመን ከፍተቶችን ከመድፈን ባለፈ በተለይ የግብርና ዘርፉን ምርታማነት የበለጠ በማሳደግና የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማስፋት ርብርብ ይደረጋል ብለዋል፡፡ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈጻጸም ላይ የሚካሄደው ውይይት በቀጣይም ከባለሃብቱና ከሲቪክ ማህበራት ጋር በተመሳሳይ ይካሄዳል፡፡
መጣጥፍ
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 2267
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ)
Jan 25, 2023 2315
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ) አየለ ያረጋል (ኢዜአ) መዳረሻዬ ሽሬ እንዳስላሴ ነው። ለዘገባ ሥራ ከባህርዳር- ጎንደር- ደባርቅ- ሸሬ መንገድ ከሚዲያ ባልደረቦች ጋር እየተጓዝኩ ነው። የጥምቀት ሙሽራዋ ጎንደር እየተኳኳለች ነበር። ደባርቅ ከመድረሴ በፊት ዳባት ትገኛለች-የደጃች አያሌው ብሩ ቁርቁር ከተማ። ደጃች አያሌው ትውልዳቸው በጌምድር ጋይንት ቢሆንም ግዛታቸውና ኑሯቸው ዳባት ነበር። ሞገደኛው ደጃዝማች አያሌው ብሩ በጎንደር ማኅበረሰብ ዘንድ ዝናቸው የናኘ ነው። ደጃዝማች አያሌው በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ (ከልጅ ኢያሱ እስከ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ-መንግሥት) ታሪካዊ ክንውኖች ጉልህ ተሳትፎ አላቸው። አንዷን ብቻ ልምዘዝ። ራስ ተፈሪ ‘ንጉሠ-ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ’ ደጃች አያሌው የቅርብ ዘመዳቸውን ራስ ጉግሳ ወሌ ብጡልን (የንግሥት ዘውዲቱን ባለቤት) ወግተው የጎንደር ግዛት ‘ራስ’ ተብለው ለመሾም ቃል ቢገባላቸውም፤ ተልዕኳቸውን ተወጥተው ቃሉ ባለመፈጸሙ ደጃዝማቹ ከአጼው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። በዚህም:- "አያሌው ሞኙ፣ ሰው አማኙ ሰው አማኙ፣ የአያል ጠመንጃ፣ ስሟን እንጃ ስሟን እንጃ…” በማለት የጎንደር አዝማሪ አዚሟል። ዛሬም ይህ ግጥም የብዙ ባህላዊ ዘፈኖች አዝማች ነው። ደጃች አያሌው ብሩ ደፋር ናቸው ይባላል። ከአጼ ኃይለሥላሴ ጋር ቢቀያየሙም በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ሲመጣ ቅድሚያ ለአገሬ ብለዋል። ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘው የዶክተር ሀራልድ ናይስተሮም (ትርጉም ገበየሁ ተፈሪ እና ደሳለኝ አለሙ) መጽሐፍ እንደተጠቀሰው ደጃች አያሌው “ንጉሡ እንደኛ ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ ግን የሁላችንም ናት" ብለው ጦራቸውን መርተው በሽሬ ግንባር ዘምተዋል። ጉዟችን ቀጥሏል። ደባትን እያለፍን ነው። ‘እንኳን ደህና መጡ፤ ወደ ጭና ታሪካዊቷ ሥፍራ’ የምትለዋን ታፔላን በስተግራ እያየን ወደ ደባርቅ ገሰገስን። የሰሜን ተራሮች የብርድ ወጨፎ ያረሰረሳትን ደባርቅን ከማለፋችን ሊማሊሞ ጠመዝማዛ ቁልቁለት ተቀበለን። አስፈሪ የሊማሊሞ መልክዓ ምድር የደጋው ሰሜን ውርጭ እና የተከዜ በርሃ ኬላ ነው። ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድህን “የሰማይ የምድሩ ኬላ፣ የየብስ የጠፈሩ ዋልታ አይበገር የዐለት ጣራ፣ አይመክተው መከታ ሊማ-ሊሞ አድማስ ሰበሩ፣ በጎማ ፈለግ ይፈታ? በትሬንታ እግር ይረታ?…” ብሎ የመኪና መንገድ ተገንብቶበት በማየቱ ግርምቱን የተቀኘለትም ለዚህ ይመስላል። ከሊማሊሞ ቁልቁለት በኋላ አዲ-አርቃይ፣ ዛሪማ፣ ማይፀብሪ እና ሌሎች የጠለምት ወረዳ ከተማዎችን አልፈን፤ የዋልድባ ረባዳማ አካባቢዎችን ተሻግረን ተከዜ ወንዝ ደረስን። የዚህን መንገድ እና ተከዜ ወንዝን ሳስብ የሀዲስ ዓለማየሁ ትዝታ አስተከዘኝ። የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ጦር የወገንን ጦር ፊት ለፊት መቋቋም ሲሳነው በሰው ልጆች ላይ ተደርጎ የማያውቅ መርዝ በጅምላ የፈጀበት አሳዛኝ ታሪክ ነበር። በተከዜ ወንዝ ውሃን በመመረዝ የወገን ጦር ያለቀበት ሥፍራ ነው። የተከዜ ሸለቆ በኢትዮጵያዊያን ደምና አጥንት ዋጋ የተከፈለበት ነው። ሀዲስ ዓለማየሁ በአንድ ዕለት የተመለከቱትን እንዲህ ጽፈውታል። “የተከዜ ውሀ እመሻገሪያው ላይ ሰፊና ፀጥ ያለ ነው። ታዲያ ያ ሰፊ ውሀ፤ ገና ከሩቅ ሲያዩት ቀይ ቀለም በከባዱ የተበጠበጠ ይመስላል። “ምን ነገር ነው፤ ምን ጉድ ነው?” እየተባባልን ቀረብ ስንል መሻገሪያው በቁሙም በወርዱም ከዳር እስከ ዳር ሬሳ ሞልቶበት የዚያ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው። የሰው ሬሳ፣ የፈረስ እና የበቅሎ ሬሳ፣ ያህያ ሬሳ፣ ያውሬ ሬሳ፥ ሬሳ ብቻ! እግር ከራስ ራስ ከእግር እየተመሰቃቀለ እየተደራረበ ሞልቶበት፥ የዚያ ሁሉ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው”። ይሉናል። ቀጥለውም “በእውነቱ እንዲህ ያለውን መሳሪያ ምንም ጠላት ቢሆን በሰው ላይ ለማዋል የሚጨክን ሰው፥ ሰብዓዊ ስሜት የሌለው፣ አለት ድንጋይ የተፈጠረበት መሆን አለበት፤ እንዲህ ያለውን መሳሪያ በሰው ላይ ማዋል ሰብዓዊ ህሊና ሊሸከመው የማይችል እጅግ ከባድ መሆኑን ዓለም ሁሉ ያወቀውና ያወገዘው በመሆኑ የኢጣሊያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ከማድረጉ በቀር “ሌላ መንግሥት በሌላ አገር ላይ አደረገ’ ሲባል ተሰምቶ የሚያውቅ አይመስለኝም” ብለዋል። ከተከዜ ባህር ማዶ ጉዞዬ ያገኘኋት ሌላዋ ታሪካዊ ሥፍራ እንዳባጉና ናት። እንዳባጉና የወገን ጦር ትልቅ ገድል የፈጸመበት ነው። ጀግኖች አባቶቻችን የጠላት ታንክ ሳያስፈራቸው የጠላት ጅምላ ጨራሽ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ተቋቁመው ጠላትን ድባቅ የመቱበት፤ ወደ አክሱም እንዲያፈገፍግ ያደረጉበት ሥፍራ ነው። “የጠላት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በጦር ሜዳው ትንንሽ ቦምቦች አውቶማቲክ ጠመንጃ ይተኩስ ነበር። አቢሲኒያኖች ደግሞ ከጠላት ጋር ግብግብ ገጥመው ጉዳይም አልሰጡትም ነበር…” ይላል ዶክተር ሀራልድ ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘ መጽሐፉ። ይህ አካባቢ በሀገር ፍቅር የነደዱ ኢትዮጵያዊያን ደም ያፈሰሱበት፣ አጥንት የከሰከሱበት፤ ለኢትዮጵያ መስዕዋትነት የከፈሉበት ነው። ይህ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ቀጣና ነው። ቀኑ ተገባዷል። ጉዟችን እንደቀጠለ ነው። እኔም የማሽላ ማሳዎችን ግራ ቀኝ እየተመለከትኩ ለዕለቱ መዳረሻችን ወደሆነችው ሽሬ ከተማ ገባን። ሽሬ በትግርኛ ‘ሽረ’ ሲሉት ይደመጣሉ። በእርግጥ ሽሬን ለመጀመሪያ ጊዜ መርገጤ ነው። ዕለቱም ጥር ሥላሴ ነው። ሽሬ በጥር ሥላሴ ትደምቃለች፤ ሙሉ ስሟም ሽረ እንዳስላሴ ነው። የሽሬ ሥላሴ ጠበል ሽሬ ደርሰን ማረፊያችንን ያዝን። ጊዜው በጣም አልመሸምና ከተማዋን በቀላሉ መቃኘት ይቻላል። ሽሬ ሰፊና ደማቅ የዞን ከተማ ናት። ከመካከላችን የአንደኛው ባለሙያ ቤተሰቦች ሽሬ ነበሩና አስጠሩን። ለሥላሴ ጠበል ግብዣ። ባል እና ሚስቱ ከልክ በላይ መስተንግዶ አደረጉልን። ‘ጠብ እርግፍ አድርገው አስተናገዱን’ ማለት ይቀላል። እንግዳ መቀበል ነባር ኢትዮጵያዊ እሴታችን ቢሆንም ጦርነት ውስጥ ለቆየ አካባቢ የተለየ መልክ ነበረው። እንግዳ አቀባበላቸው በእርግጥም የመሃል አገር ሰው የናፈቃቸው ይመስላል። የተትረፈረፈ እህልና ውሃ አቅርበው በ’ብሉልን፤ ጠጡልን’ ተማጽኗቸው የተነፋፈቀ ቤተ-ዘመድ ግብዣ አስመሰሉት። የሥላሴው ጠበል የሸሬ ጠላ ቀረበ። የሸሬ ጠላ ሳስታውስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ታወሱኝ። የወቅቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምሀሩ ፕሮፌሰር ሽብሩ በዘመነ ደርግ በዕድገት በሕብረት ዘመቻ ተማሪዎቻቸውን ይዘው ሽሬ ዘምተው ነበር። በወቅቱ ታዲያ የሸሬ ጠላ ፍቅር ይዟቸው በየጊዜው ሲኮመኩሙ የተመለከቱ ሰዎች ‘ፕሮፌሰሩ ከጠፉ የሚገኙት ጠላ ቤት ነው’ ሲባሉ እንደነበር ‘ከጉሬ ማርያም እስከ አዲስ አበባ’ በተሰኘው ግለ ታሪካቸው አስፍረዋል። ከግብዣ መልስ ከማረፊያ ሆቴል ላይ ሆኜ ከተማዋን ስቃኛት ከጦርነት ድባቴ የተላቀቀች ይመስላል። የአመሻሽ ሕዝቡ እንቅስቃሴም ሆነ እስከ ሌሊቱ አጋማሽ የሚሰሙ የመዝናኛ ቤቶች ሙዚቃዎች የከተማዋን አሁናዊ መልክ የገለጠልኝ ነበር። ንጋት ላይ በቁርስና ቡና ሰዓታት ከሰዎች ጋር መስተጋብሬ ጀመረ። በጦርነት አዙሪት የከረመችው ሽሬና አካባቢው ኑሮ እጅጉን የከበደ ነበር። መልከ-ብዙ ማህበራዊ ቀውሶች አስተናግደዋል። አሁናዊ ምላሻቸው “ተመስገን፤ ያ ሁሉ አለፈ” የሚል ነው። ገበያው ተረጋግቷል፤ ማህበራዊ ኑሮ ተመልሷል። ድህረ-ሰላም ስምምነት ለሽሬ ነዋሪዎች ሁለንተናዊ እፎይታን አንብሯል። ከቀናት በኋላ በአክሱም የታዘብኩትም እንዲህ ነው። ኑሮን ያቀለለው የተቋማት አገልግሎት ጅማሮ በመጀመሪያ ዘገባ ስራዬ መሰረተ ልማትን አገልግሎት ቃኘሁ። ባንክ፣ ቴሌ፣ ሆስፒታል… መሰሎቹን። ተጠቃሚዎችንም፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ስራ ሃላፊዎችንም አነጋገርሁ። ከሰላም ስምምነቱ ማግስት ጀመሮ ተቋማቱ ወደስራ መመለሳቸው ከሁለንተናዊ ችግር እንደታደጋቸው ያነሳሉ። በትራንስፖርት እየተንቀሳቀሱ፣ በኤሌክተሪክ ስራዎቻቸውን እየከወኑ ነው። ለሁለት ዓመታት የተቋረጠው አገልግሎት አቅርቦት እና የአገልግሎት ፈላጊዎች ፍላጎት ግን አሁንም ሙሉ በሙሉ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ የተጠቃሚዎችም፤ የአገልግሎት ሰጭዎችም ሀሳብ ነው። በሽሬ ስሁል ሆስፒታል የተመለከትኳቸው፤ ያነጋገርኳቸው፤ ከታዳጊዎች እስከ አዛውንት ዕድሜ ያሉ ህሙማን የሰላም አየር ማግኘታቸው የሕይወታቸው ዑደት እንዲቀጥል አድርጓል። ድንገተኛም ሆነ ነባር ህመም ያለባቸው ሰዎች በነጻ እየታከሙ ነው ያገኘኋቸው። ሰላም ከሌለ መታከም ቀርቶ በቅጡ ማስታመም፤ በወጉ መቀበርም እንደማይቻል ገልጸውልናል። የጤና፣ የባንክና የቴሌኮም አገልግሎት የግብዓት ክፍተቶች የማሟላት ሰራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም በፌዴራል ደረጃ በየተቋማቱ የተመደቡ አስተባባሪዎች አረጋግጠውልኛል። የጸጥታ አካሉና የህብረተሰቡ ትብብርም የሚያስቀና እንደሆነ ግለሰቦችም፤ የጸጥታ አካላትም ነግረውኛል። አክሱም ጺዮን ማርያም፣ ሽሬ ስላሴ ንግስ፣ የጥምቀት በዓላት ከሶስት ዓመታት በኋላ በአደባባይ ታቦት ወጥቶ ተከብሯል። የፌዴራል ፖሊስ ተወካዮችም ይህንኑ ነው ያረጋገጡልኝ። የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከከተማ ነዋሪዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት ቤተሰባዊ የሆኑ ይመስላል። እንቅስቃሴያቸውም የሰላማዊ ቀጠና መልክ ያለው ነው፤ ዩኒፎርም ከመልበሳቸው በስተቀር ጀሌያቸውን ይንቀሳቀሳሉ። ይህ ደግሞ መተማመን ከመፍጠር ባለፈ ጦርነት ውስጥ ለቆየ ማህበረሰብ ከስነ ልቦና ጫና እንዲላቀቅ አይነተኛ ሚና እንደላው ይሰማኛል። ኢ-መደበኛ የሽሬና አክሱም ወጎች ያረፍኩበት ሆቴል ባለቤት ‘አደይ’ ተግባቢ ናቸው። ደግ እናት ይመስላሉ። ከገባን ጀምሮ ‘ጠላ ተጎንጩ፤ ቡና ጠጡ’ ጭንቃቸው ነው። ሁለት ቀን ቡና አስፈልተውልናል፤ ጠላ አቅርበው ዘክረውናል። ይህ ሁሉ ሲሆንም ለከተማው እንግዳ መሆናችንን እንጂ ስለሙያችንም ሆነ ስለሌላ ማንነታችን አያውቁም ነበር። ብዙ መጨዋወትና ውሎ አዳር በኋላ ነው ጋዜጠኛ ስለመሆናችን ያወቁት። አደይ ተጨዋች ናቸው። አማርኛ ያዝ ቢያደርጋቸውም ጨዋታቸው ‘ኩርሽም’ ነው- ተሰምቶ የማይሰለች። በአጋጣሚ ‘ሰለክላካ’ ስለምትባለዋ ታሪካዊ ሥፍራ ጠይቄያቸው እያወጋን ነበር። ‘እንደእናንተ ወጣቶች ሳለን ‘ሰለክላካን ያላዬ ሸዋን ያመሰግናል’ ይባል ነበር። ታዲያ አንድ የሸዋ ሰው መጣና ሰለክላካን አየና ‘በቃ ይቺ ናት’ ሰለክላካ’ ብሎ ተገረመ” ብለው አሳቁን። (የፍቅር እስከ መቃብር መሪ ገጸ-ባህሪው ‘በዛብህ’ ወደ ዲማ ጊዮርጊስ ሄዶ ‘የዲማ መልኳ እና ዝናዋ’ ተጣርሶበት እንደተገረመበት ቅጽበት መሆኑ ነው)። አደይ የተጀመረው ሰላም ፍጹም ምሉዕ ሆኖ ወደ ቀደመ ኢትዮጵያዊ መልካችን የምንመለስበት ጊዜ እንዲመጣ ይሻሉ። ከጦር-ነት ወደ ሰላም-ነት! ቆንጂዬዋ ፊዮሪ የኮሌጅ ተማሪ ነበረች። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጀምሮ በኋላም በጦርነት ሳቢያ ትምህርቷን ካቆመች ሦስት ዓመታት ሆኗታል። ጦርነቱ ከቆመ በኋላ የጀበና ቡና ጀምራለች። ደንበኞቿ ሰብሰብ ብለን እንቀመጣለን። ፊዮሪ ከስኒ ማቅረቢያዋ ላይ አነስተኛ ጀበናዋን፤ የሚያማምሩ ስኒዎቿን እና መዓዛው ከሚያውድ የዕጣን ማጨሻዋ ጋር ሰድራ ይዛ ትቀርባለች። ከመካከላችን ካለው ጠረጴዛ ላይ ታስቀምጥና እርሷም ወንበር ይዛ ከመካከላችን ትቀመጣለች። ቡናው እስኪሰክን ጨዋታዋን ታስኮመኩመናለች። ቡናው ከሰከነ በኋላ ቡናዋን ቀድታ ለእያንዳንዳችን በእጃችን እያነሳች ትሰጣለች። በሽሬ ቡና የሚቀርበው በዚህ መልክ ነው። ለፊዮሪ እና መሰሎቿ ጦርነቱ ክፉ ጠባሳ መጣሉ፤ ተስፋቸው ላይ መጥፎ አሻራ ማስቀመጡን ታነሳለች። አሁን ግን ብሩህ ተስፋ ሰንቃለች። ስለነገዋም “ሰላሙ ይዝለቅልን፤ ትምህርቴን ለመቀጠል እመኛለሁ” ትላለች። አክሱም ከሽሬ በስተሰሜን 60 ኪሎ ሜትር ይርቃል። ከሽሬ አክሱም ስንንቀሳቀስ ከጥምቀት ዕለት በስተቀር ገበሬው የግብርና ሥራዎቹን እየከወነ ነበር። አርሶ አደሩ ያርሳል፤ መስኖውን ያለማል። የተዘራውን ውሃ ያጠጣል። የበቀለ ቡቃያውን ይኮተኩታል። ከጦርነት ወደ ልማት መዞሩን ዐይኔ ታዝቧል። በጥምቀት ዋዜማ፤ የከተራ በዓል ዕለት ሁለት ጎራማይሌ የረፋድ ትዕይንቶችን ላንሳ። ከአክሱም ከተማ ወደ አድዋ እና ሽሬ መገንጠያ አካባቢ ሰፊ የቀንድ ከብት ገበያ ነበር። እውነተኛ የዓመት በዓል ገበያ መልክ ያለው ትዕይንት ነበር። በተለይም የፍየል ዋጋ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተገበያዩ እንደነበር ሰምቻለሁ። ታሪካዊቷን አክሱም ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ የረገጥኳት/የተሳለምኳት ከአራት ዓመት በፊት በ2011 ዓ.ም ይመስለኛል። ከገበያው ቀጥሎ በታቦተ-ጽዮን መገኛዋ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ደጅ፣ በጥንታዊያኑ የአክሱም ሐውልት መገኛ አደባባይ ነበር። ከጽዮን በስተምዕራብ በአርባቱ እንሰሳ በኩል፤ በቅዱስ ያሬድ ዋርካ… አድርጌ በጽዮን ዋናው በር ደረስኩ። ማራኪ የአክሱም የኮብልስቶን መንገዶች ኦና ናቸው። የወትሮው ግርግር ናፍቋቸዋል። ከጽዮን ቅጥር ግቢ በዋናው በር በስተውጭ አነስተኛ እና ብቸኛ ዋንዛ በኮብልስቶን መሃል ነበረች። ዛሬም ለምልማ አለች። በዚህ አካባቢ ድሮ የነጭ ጎብኚ ጋጋታ፣ የጽዮን ደጅ ጠኚ ምዕመን… የተጨናነቀ ነበር። እንደ ድሮው የፎቶ አንሺ ግርግር፣ የአክሱም መስቀል ቀርጸው የሚሸጡ ወጣቶች ጫጫታ የለም። ይልቁንም እርጥባን የሚሹ አቅመ ደካሞችና ህፃናት ነበሩ። ጦርነት የሥፍራዋን መልክ አጠይሞታል። ያም ሆኖ ከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ሙሉ በኩሉሄ ባይባልም ወደነበረበት እየተመለሰ ነው። የግልም ሆነ የመንግሥት ባንኰች ሥራ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከአክሱም ሐውልት ወደ ሌላ ሰፈር አቀናሁ። ትርሐስ ገና ታዳጊ ልጅ ነች። ጠይም፤ ስርጉድ፣ ሳቂታና ተረበኛ አይነት ልጅ ነች። እንደ ሽሬዋ ፊዮሪ መንገድ ዳር የጀበና ቡና እየሰራች ነው። ከሩቅ የመጣን እንግዶች መሆናችንን ስታውቅ፤ ደስታዋ ከገጿ ይነበብ ነበር። ያለፉ ጊዜያትን ሰቆቃ አጫወተችን። ስለቀጣይ ዕጣ ፈንታዋ እና ዕቅዷ ስታወራ ትቆይና “የሰው ልጅ ግን በጣም ከሃዲ ነው። ከወራት በፊትኮ ስለቢዝነስ አላስብም ነበር። መቼ እሞታለሁ እንጂ” ብላ ራሷን ትወቅሳለች። ወደ ሰማይ አንጋጣ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች። ጦርነት ተራውንም ሕዝብ ለመልከ-ብዙ ቀውስ ዳርጎት እንደቆየ ታነሳለች። ዛሬ ሁሉ አልፎ ሰላም መውረዱ ለመጨዋወት መብቃቷ ለእርሷ ትልቅ ብሥራት ነው። ይህ ለትርሐስ ብቻ ሳይሆን ለመላው አክሱማዊያን መሆኑ እሙን ነው። አክሱም ከተማ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ከዋለችበት ጊዜ ጀምሮ በከተማዋ በሻለቃ አዛዥነት የተሰማራ የፌደራል ፖሊስ አባልም ያጋጠመውን አሳዛኝ ገጠመኞች አጫውቶኛል። ጦርነቱ ቢራዘም ኖሮ በተራው ሕዝብ ላይ ምን ያህል የከፋ ጉዳት ይደርስ እንደነበር በአሳዛኝ ሁኔታ ገልጾልኛል። አክሱሞች ያን ሁሉ አልፈው ሰላም አየር ነፍሶ፣ ከስጋት ቆፈን ተላቀው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ተመልሰዋል። የዛሬ ሳምንት ሰርክ(11 ሰዓት) ላይ አክሱም የከተራ በዓል በድምቀት አክብራለች። ታቦተ-ጽዮን ወደ ባህረ- ጥምቀቱ ስትወርድ፤ ወግና ሥርዓቱ ተጠብቆ፣ ሕዝቡ በሀበሻ ነጫጭ አልባሳት፣ ካህናት በልብሰ ተክህኖ ደምቀው … እየተከወነ ነበር። አንዲት እናት ለአማርኛ ተናጋሪ በቀረበ አነጋገር እያለቀሱ ታቦት እየሸኙ ነው። ትኩር ብዬ ሳያቸውም ዕንባቸው ዱብ ዱብ ይላል። “ከዚያ ሁሉ መከራ አልፎ ለዚህ በቃን፤ ተመስገን” እያሉ እልልታውን ያቀልጡታል። በደስታ እያነቡ ነበር። ይህ ስሜት የብዙኃኑ አክሱማዊያን እናቶች እንደሆነ መገመት ቀላል ነው። አክሱም በኮቪድ እና በኋላም በጦርነቱ ምክንያት ባህረ-ምቀት ታቦት ወጥቶ ሲከበር ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ከወትሮው በተለየ ድምቀትና ውበት በሰላምና በደስታ፤ በአደባባይ እልልታና ሆታ በማክበራቸው ልዩ ስሜት ፈጥሮባቸዋልና! እናም በአክሱም የከተራ ሆነ የበዓለ-ጥምቀት ክብረ-በዓላት በሰላም ስምምነቱ ማግስት በድምቀት ተከውኖ አለፈ። የሃይማኖት አባቶቹም ሆኑ ምዕመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅም የዘንድሮው ክብረ-በዓል ካለፉት ዓመታት ነባራዊ ሁኔታ ጋር እያነጻጸሩ፤ ትልቅ ብሥራትና መልክ እንዳለው ገልጸዋል። ሰላም እንዲጸና፤ ነባር ኢትዮጵያዊ አንድነትና መተባበር እንዲመለስ ጽኑ መሻታቸውን ነግረውናል። በበጎ ቀን የማውቃትን አክሱም፤ ከረዥም ጊዜ በኋላ አሁናዊ መልኳን ታዝቤ፤ የነገ ትዝታ ሰንቄ ተመለስኩ!! ሰላም ለኢትዮጵያ!!
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም