ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በዞኑ ከ12 ሺህ 600 ቶን በላይ የማር ምርት ለገበያ ይቀርባል
Jan 9, 2026 26
ነቀምቴ ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ወለጋ ዞን በበጀት ዓመቱ 12 ሺህ 674 ቶን የማር ምርት ለገበያ እንደሚቀርብ የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት አስታወቀ። በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የልማት ኢንሼቲቭ ተቀርጾላቸው በአዲስ መልክ እየተሰራባቸው ካሉ የግብርና ስራዎች መካከል የማር ልማት አንዱ ነው። የምስራቅ ወለጋ ዞን ለማር ልማት አመቺ ከሚባሉት የክልሉ ዞኖች አንዱ ነው። በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የእንስሳት እንክብካቤና ልማት ክፍል ሃላፊ አቶ አዲሱ ዳቤ፣ በዞኑ የሚገኘውን ምቹ የአየር ሁኔታ እና የደን ሀብት በመጠቀም የማር ምርት መጠንን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።   በተያዘው በጀት ዓመትም 12 ሺህ 674 ቶን ለገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አንስተው በእስካሁኑ እንቅስቃሴ ከ8 ሺህ ቶን በላይ የማር ምርት ለገበያ መቅረቡን ገልጸዋል። በዘርፉ የተያዘው እቅድ እንዲሳካም ዘመናዊ ቀፎዎች ለአርሶ አደሩ በስፋት እንዲቀርቡ መደረጉንም ነው የገለጹት። በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ 2 ሺህ 500 ዘመናዊ ቀፎዎች ለአርሶ አደሩ የቀረበ ሲሆን በድምሩ በ38 ሺህ 147 ተሸጋጋሪ ቀፎ እና በ84 ሺህ 961 ባህላዊ ቀፎዎች የንብ ማነብ ስራው እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። በዞኑ ከ26 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በንብ ማነብ ስራ መሰማራታቸውን ገልጸው አብዛኞቹ ማር አምራቾች በዞኑ ዲጋ ወረዳ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የዲጋ ወረዳ የግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ይስሐቅ አዲሱ፣ በወረዳው በ22 ሺህ 500 ዘመናዊ ቀፎ የንብ ማነብ ስራ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።   በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 820 ቶን ማር ተመርቶ ለገበያ መቅረቡን አንስተው በወረዳው 13 ሺህ 760 አርሶ አደሮች በንብ ማነብ ስራው ተሰማርተው ይገኛሉ ብለዋል። በማህበር ከተደራጁ ማር አምራች የወረዳው አርሶ አደሮች መካከል ማሞ ኡመታ እና ጓደኞቻቸው ሰባት ሆነው በ50 ዘመናዊ ቀፎ የንብ ማነብ ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ። ባለፈው ዓመት 120 ኪሎ ግራም ለገበያ ማቅረባቸውን ተናግረው በዚህ ዓመት 200 ኪሎ ግራም ማር ለገበያ ለማቅረብ እየተዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው የወረዳው ነዋሪ አቶ ብርሃኑ ሂንኮ፤ ባላቸው ሰባት ዘመናዊ ቀፎ የንብ ማነብ ስራ እያከናወኑ ሲሆን ዘንድሮም 40 ኪሎ ግራም ማር ለገበያ ማቅረባቸውን ተናግረዋል።
በንጋት ሰው ሰራሽ ሐይቅ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚዎች ምቹ የልማት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቷል
Jan 9, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የንጋት ሰው ሰራሽ ሐይቅ ላይ በቱሪዝም ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚዎች ምቹ የልማት ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር ገለጸ። የለውጡ መንግስት ቱሪዝምን ከአምስቱ ግንባር ቀደም የኢኮኖሚ ምሰሶዎች መካከል በማድረግ ለቅርስ ጥበቃ፣ ዕድሳትና ለአዳዲስ የመዳረሻ ልማት የሰጠው ትኩረት ዘርፉ እንዲያንሰራራ አስችሏል። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በርካታ ቀልብን የሚስቡ ታሪካዊ፣ ኃይማኖታዊ፣ ባህላዊና ተፈጥሯዊ የመስህብ ዕምቅ ጸጋዎችን የታደለች ሀገር ናት።   ከቅርብ ዓመታት ወዲህም የኢትዮጵያን ዕምቅ የመስህብ ጸጋዎች በመንከባከብና በማልማት የቱሪዝም ሃብት ወሳኝ የኢኮኖሚ አቅም እንዲሆን እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተገነቡ ማራኪ የመዳረሻ ሥፍራዎችም ለጎብኝዎች ምቹ ምኅዳርን በመፍጠር የቱሪዝም ተወዳዳሪነትን በእጅጉ እያሳደጉ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቱሪዝም፣ የዓሳ ሃብት ልማት፣ የውሃ ላይ ትራንስፖርትና መሰል የመስህብ መዳረሻ ኢንቨስትመንትን ማሳደግ የሚያስችል ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱንም አስረድተዋል። በሕዳሴ ግድብ የንጋት ሐይቅ እና ዙሪያውን ለማልማት የተዘጋጀው ፍኖተ ካርታ የግሉን ዘርፍ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ተሳትፎ የሚያሳድግ ዕድል መፍጠር እንደቻለ ገልጸዋል።   ለዚህም የግሉ ዘርፍ በንጋት ሐይቅ የቱሪዝም ልማት ኢንቨስትመንት ተሳትፎን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት፣ ከፌደራልና ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መንግስት ጋር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በንጋት ሐይቅ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ለሚሳተፉ አልሚዎችም የግንባታ መሳሪያ፣ ተሽከርካሪ እና መሰል ቁሳቁሶች ከቀረጥ ነፃ አገልግሎት የሚያገኙበት ዕድል መመቻቸቱን አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በየዘርፉ ለሚዘጋጁ እቅዶች፣ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ትክክለኛ ግብዓት ያስገኛል
Jan 9, 2026 27
ሐረማያ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በየዘርፉ ለሚዘጋጁ እቅዶች፣ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ትክክለኛ ግብዓት እንደሚያስገኝ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ገለጸ። አገልግሎቱ ለሁለተኛ ዙር የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የአሰልጣኞች ስልጠና በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ባለሙያዎች በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እየሰጠ ነው። በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከፍተኛ የስታቲስቲክስ ባለሙያ እና በስልጠናው የቴክኒክ ዋና አስተባባሪ ሃይሌ ዓለሙ እንዳሉት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዘርፈ ብዙና የተለያዩ መረጃዎችን ይሰበስባል፤ ይተነትናል።   የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን ለሚያደርጉ ባለሙያዎችም የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው፤ በስልጠናው የኢኖሚ ድርጅቶች ትርጉም፣ ጽንሰ ሃሳብ፣ ዓላማና ሌሎች መረጃ ለመሰብሰብ የሚያገለግሉ ሃሳቦችን የሚገነዘቡበት መሆኑን ተናግረዋል። የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ዓላማም የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሃብት ደረጃ ለማወቅና ድርጅቶችን በዓይነት፣ በብዛትና በደረጃ ለመለየት እንዲሁም ለጥናትና ምርምር፣ ለፖሊሲ፣ ለስትራቴጂና እቅድ ዝግጅት ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች አሉት ብለዋል። በአገልግሎቱ የሐረር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ሙክታር ጀማል እንደገለጹት በቅርንጫፉ አስተባባሪነት ከሐረር፣ ድሬዳዋ፣ ጭሮ፣ ጎዴና ጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ለተውጣጡ 180 ሰዎች የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ተጀምሯል።   የአሰልጣኞች ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚቆይ ጠቁመው፤ ስልጠናው ጥራትና ወቅቱን የጠበቀ፣ ተገቢነትና ተአማኒነት ያለው መረጃ መሰብሰብ የሚያስችል ክህሎት እንዲያገኙና ሌሎችን እንዲያበቁ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።
በክልሉ በጤና ተቋማት ወቅቱን የተከተለ የዲጂታል አሰራርን በመተግበር የእናቶችን ጤና ለመጠበቅ ትኩረት ተደርጓል
Jan 9, 2026 49
ሰመራ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በጤና ተቋማት ወቅቱን የተከተለ የዲጂታል አሰራርን በመተግበር የእናቶችን ጤና ለመጠበቅ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለፀ። ቢሮው "ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለእናቶች ጤና" በሚል መሪ ሐሳብ ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ አንድ ወር በተለያዩ ኹነቶች የሚከበረውን የእናቶች ጤና ወርን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ዊቲካ ኖሬ በመግለጫቸው እንዳሉት የእናቶችን ጤና መጠበቅ ሲቻል የቤተሰብና የህብረተሰብ ጤና የተጠበቀና ጤናማ ትውልድ ማፍራት ያስችላል። በዚህም በቀጣይ በሚከናወኑ ኹነቶች ፈጠራና ክህሎትን በማሳደግ እንዲሁም በጤና ተቋማት የማዋለጃ ቁሳቁሶችን ማዘመንና ወቅቱን የተከተለ የዲጂታል አሰራር ላይ ትኩረት በማድረግ ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል። ዘላቂነት ያለው የገንዘብ ምንጮችን በማጎልበት በእናቶች ደህንነት እና ጤና ላይ ከአጋር አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራም አስረድተዋል። በተለይም አቅመ ደካማ እናቶችን በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ ከባለሃብቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር በመስራትና በአካባቢ ያለን ፀጋ በመጠቀም የገንዘብ ማግኛ አማራጮችን የማስፋት ስራም ይሰራል ብለዋል። በዚሁ በእናቶች ወር ከሚከናወኑት የንቅናቄ ስራዎች መካከል በተለይም የአርብቶ አደሩ አካባቢ እናቶች በጤና ተቋማት ብቻ እንዲወልዱና የህክምና ክትትላቸውን እንዲያደርጉ ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እንደሚሰራም ገልጸዋል። በተጨማሪም ከተንቀሳቃሽነት የኑሮ ዘይቤ ይልቅ በቋሚ ስፍራ እንዲኖሩ የሚያስችሉ ተግባራትም በትኩረት ይከናወናሉ ብለዋል። በክልሉ የጤና ክትትል የሚደረግላትና ደህንነቷ የተጠበቀ እናት እንድትኖር የሚከናወኑ ተግባራት እንዲጠናከሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል። በቅርቡ የተከፈተው የዱብቲ የእናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከልን እንደ አብነት ያነሱት ምክትል ሃላፊው፤ መሰል የጤና ተቋማትን ማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት መሆኑን ገልፀዋል። በእናቶች ጤንነትና ደህንነት ላይ የሚሰሩ ስራዎች መመዝገብ፣ መከታተልና ማስቀመጥ ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚከናወንም ነው ያስረዱት።      
በክልሉ በአፈር አሲዳማነት የተጠቃ መሬትን በተፈጥሮ ማዳበሪያና በኖራ በማከም ወደ ምርት ለማስገባት እየተሰራ ነው
Jan 9, 2026 41
አዳማ፤ ጥር 1/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በአፈር አሲዳማነት የተጠቃ መሬትን በተፈጥሮ ማዳበሪያና በኖራ በማከም ወደ ምርት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ። በቢሮው የአፈር ለምነት ማሻሻያ ዳይሬክተር አቶ እሸቱ ለገሰ ለኢዜአ እንደገለጹት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የአፈር ለምነትና ጤንነት የመጠበቅ ስራ ትኩረት አግኝቷል። በተለይም በአሲድ የተጠቃ መሬትን በተፈጥሮ ማዳበሪያና በኖራ ለማከም ለአርሶ አደሩ ግንዛቤና ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል። በክልሉ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ለአፈር አሲዳማነት ተጋላጭ መሆኑን አንስተው ችግሩን ለመቅረፍም መሬቱን በተፈጥሮ ማዳበሪያና በኖራ ለማከም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የተፈጥሮ ማዳበሪያውም በኮምፖስትና በቨርሚ ኮምፖስት እንዲሁም የባዮ ጋዝ ተረፈ ምርቶችን በመጠቀም እየተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ በእስካሁኑ ሂደትም ከ100 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ አገልግሎት ላይ እየዋለ ይገኛል ብለዋል። የኖራ አቅርቦትን ለማሳደግም በጉደር የኖራ ፋብሪካ በቀን 800 ኩንታል ኖራ የመፍጨት አቅም ያላቸው ሁለት ወፍጮዎችን የመትከል ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። የምዕራብ አርሲ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት የአፈር ለምነት ቡድን መሪ አቶ አብደላ ኢብራሂም እንደገለጹት በዞኑ 100 ሺህ ሄክታር የሚሆን መሬት በአፈር አሲዳማነት መጠቃቱን ተናግረዋል። መሬቱን ወደ ለምነት ለመመለስም ባለፈው ዓመት 25 ሺህ ኩንታል ኖራ ለአርሶ አደሩ በማሰራጨት በአሲዳማነት የተጠቃውን መሬት የማከም ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። ከኖራ አቅርቦቱ በተጓዳኝ በተፈጥሮ ማዳበሪያ መሬቱን በማከም ምርታማነትን የመጨመር ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በዞን ደረጃ ከ13 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ የማዘጋጀት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።    
የሚታይ
በንጋት ሰው ሰራሽ ሐይቅ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚዎች ምቹ የልማት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቷል
Jan 9, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የንጋት ሰው ሰራሽ ሐይቅ ላይ በቱሪዝም ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚዎች ምቹ የልማት ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር ገለጸ። የለውጡ መንግስት ቱሪዝምን ከአምስቱ ግንባር ቀደም የኢኮኖሚ ምሰሶዎች መካከል በማድረግ ለቅርስ ጥበቃ፣ ዕድሳትና ለአዳዲስ የመዳረሻ ልማት የሰጠው ትኩረት ዘርፉ እንዲያንሰራራ አስችሏል። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በርካታ ቀልብን የሚስቡ ታሪካዊ፣ ኃይማኖታዊ፣ ባህላዊና ተፈጥሯዊ የመስህብ ዕምቅ ጸጋዎችን የታደለች ሀገር ናት።   ከቅርብ ዓመታት ወዲህም የኢትዮጵያን ዕምቅ የመስህብ ጸጋዎች በመንከባከብና በማልማት የቱሪዝም ሃብት ወሳኝ የኢኮኖሚ አቅም እንዲሆን እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተገነቡ ማራኪ የመዳረሻ ሥፍራዎችም ለጎብኝዎች ምቹ ምኅዳርን በመፍጠር የቱሪዝም ተወዳዳሪነትን በእጅጉ እያሳደጉ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቱሪዝም፣ የዓሳ ሃብት ልማት፣ የውሃ ላይ ትራንስፖርትና መሰል የመስህብ መዳረሻ ኢንቨስትመንትን ማሳደግ የሚያስችል ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱንም አስረድተዋል። በሕዳሴ ግድብ የንጋት ሐይቅ እና ዙሪያውን ለማልማት የተዘጋጀው ፍኖተ ካርታ የግሉን ዘርፍ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ተሳትፎ የሚያሳድግ ዕድል መፍጠር እንደቻለ ገልጸዋል።   ለዚህም የግሉ ዘርፍ በንጋት ሐይቅ የቱሪዝም ልማት ኢንቨስትመንት ተሳትፎን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት፣ ከፌደራልና ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መንግስት ጋር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በንጋት ሐይቅ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ለሚሳተፉ አልሚዎችም የግንባታ መሳሪያ፣ ተሽከርካሪ እና መሰል ቁሳቁሶች ከቀረጥ ነፃ አገልግሎት የሚያገኙበት ዕድል መመቻቸቱን አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤት አስገኝተዋል
Jan 9, 2026 77
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤት ማምጣታቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ። ሚኒስትሯ በጥር ወር የሚከበረውን "የጤናማ እናትነት ወር" አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ባለፉት ዓመታት ከወሊድ ጋር ተያይዞ የሚከሰት የጤና ችግርና ሞትን ለመቀነስ በተደረገው ርብርብ በጤና ተቋማት የሚወልዱ እናቶች ቁጥር መጨመሩን ተናግረዋል፡፡ በጤና ጣቢያዎች የቀዶ ሕክምና አገልግሎት መጀመሩ ለውጥ ማምጣቱንም ጠቅሰው የጤና ተቋማት ተደራሽነት መስፋት የቅድመ ወሊድ ክትትልን ማሳደጉንም ነው የገለጹት፡፡ ከወሊድ በኋላ የሚከሰት የደም መፍሰስን በመከላከል በኩል የበጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች ሚና እና ቁጥር ማደጉንም ተናግረዋል፡፡ እስካሁን የተገኙ ውጤቶች አበረታች መሆናቸውን ጠቁመው በቀጣይም የተሻሉ ውጤታማ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል፡፡ ለዚህም ፈጠራ እና ዘላቂ ፋይናንስ ወሳኝ መሆናቸውን ጠቅሰው የዲጂታል ጤና መረጃን ተደራሽ ማድረግ፣ የሕክምና ግብዓቶችን ማሟላትና የቀዶ ሕክምና አገልግሎትን ማስፋት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ጤናማ እናትነት አንዲት ሴት በእርግዝና፣ በወሊድና በድህረ ወሊድ ወቅት የሚኖራት ሁለንተናዊ ጤንነት ነው። የዘንድሮው የጤናማ እናትነት ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ39ኛ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ ''ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች ይከበራል።
ኢትዮጵያ በኮሪደር ልማትና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ለዓለም ተምሳሌት የሚሆን ተግባር ፈፅማለች
Jan 9, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በኮሪደር ልማትና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ለዓለም ተምሳሌት የሚሆን የላቀ ውጤት እያስመዘገበች ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩማር ራይ ገለፁ። በኢትዮጵያ ከተሞችን ለነዋሪዎች እና ለኢንቨስትመንት ምቹ የሚያደርጉ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በርካታ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በኮሪደር ልማት ከተሞችን ውብና ለኑሮ ምቹ ከማድረግ በተጨማሪ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋምና አረንጓዴ ኢኮኖሚን መገንባት የሚያስችሉ ውጤታማ ስራዎችም ተከናውነዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኒል ኩማር ራይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፣ በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ የጠንካራ ዕቅድና አፈፃፀም እንዲሁም የላቀ የአመራር ብቃት ማሳያ ነው።   በተለይም በአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብና ማራኪ ገፅታ ያላበሰ ነው ብለዋል። ይህም በኢትዮጵያ ለመኖርና ሀብት ማፍራት ለሚሹ የውጭ ዜጎችም ምቹ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውና ለተከታታይ ዓመታት የተተገበረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርም ኢትዮጵያ ተምሳሌት የሆነ ስኬታማ ተግባር ማከናወኗን አምባሳደሩ ገልፀዋል።   በዚህ ታላቅ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ በጥቂት አመታት ውስጥ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኝ በመትከል ዓለምን ያስደመመ ተግባር ያከናወነችበት ነው። በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በመላ ሀገሪቱ የአረንጓዴ ስፍራዎች እንዲበራከቱ ማድረጉን አንስተው በዚህም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ እውቅና እንድታገኝ አስችሏል ብለዋል።
የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የትውልዱ ወሳኝ የቤት ሥራ ነው
Jan 9, 2026 88
አዲስ አበባ፤ ጥር1/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ከፍተኛ እና ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያሳልጥ አስተማማኝ የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ የአሁኑ ትውልድ ወሳኝ የቤት ሥራ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን ገለጹ። በቀይ ባሕር ነባራዊ እውነታ ውስጥ ኢትዮጵያ የነበራትን ከፍተኛ ቦታ ያጣችው የህዝብ ውክልናን ችላ በማለት በተሰጠ የተሳሳተ ውሳኔ እና ሸፍጥ መሆኑ ይታወቃል። ኢትዮጵያ በተሸረበባት ታሪካዊ ሸፍጥ የባሕር በሯን በማጣቷ ላለፉት ሶስት አስርት ዓመታት በሌሎች ሀገራት ወደብ ላይ ጥገኛ እንድትሆን ተገዳለች፣ ይህ ደግሞ በኢኮኖሚ ዕድገቷና በሉዓላዊነቷ ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሯል።   የተለያዩ ሀገራት፣ የታሪክ አዋቂዎች፣ ምሁራንና ህብረተሰቡ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ብሔራዊ ጥቅምን የማስከበር ምክንያታዊና ፍትሃዊ የስትራቴጂክ ጉዳይ መሆኑን ያነሳሉ። የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አደም ካሚል ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የስልጣኔ ኃያልነት ከቀይ ባሕርና ዓባይ ወንዝ ጋር ጥብቅ ቁርኝት አለው። የውስጥ ባንዳዎችና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶች በሸረቡት ሴራ ኢትዮጵያ ከስልጣኔዋ ጋር ጥብቅ ቁርኝት ካለው አስተማማኝ የባሕር በሯ እንድትገለል መደረጉን አስታውሰዋል። በዚህም ኢትዮጵያ ላለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ዋጋ እንድትከፍል መገደዷን አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያን ከፍተኛ የህዝብ ቁጥርና ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያሳልጥ አስተማማኝ የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የአሁኑ ትውልድ ወሳኝ የቤት ሥራ መሆኑንም ገልጸዋል።   በትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር የፖሊሲና ስትራቴጂ ተመራማሪ ተመስገን ዋለልኝ(ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር ማጣት በሎጀስቲክስ እንቅስቃሴው ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለወደብ ኪራይና ትራንዚት ከምታወጣው ገንዘብ ባለፈ በወጪና ገቢ ምርቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ በማድረግ ዓለም አቀፍ የንግድ ተወዳዳሪነትን እያቀጨጨ መሆኑን ገልጸዋል። የባሕር በር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ የቀረበው ጥያቄ የሎጀስቲክስ ዘርፍ የኢኮኖሚ ስብራትን በዘላቂነት የሚጠግን ወሳኝ የዲፕሎማሲ አካሄድ መሆኑን ተናግረዋል። #Ethiopian_News_Agency  
ኢትዮጵያ እሴት የተጨመረበት ቡና ለዓለም ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ ገቢዋን ለማሳደግ እየሠራች ነው
Jan 9, 2026 80
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቡናን በጥሬው ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለዓለም ገበያ በማቅረብ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ገለጸ። ኢትዮጵያ የቡና መገኛና ከአፍሪካ ቀዳሚዋ አምራች ሀገር ስትሆን ቡናን እሴት ጨምሮ ወደ ውጭ በመላክ የተጀመረው ጥረት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው፡፡ ባለፈው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ 470 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ በመላክ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች፡፡ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት የ15 ዓመት የቡና ስትራቴጂ ፍኖተ ካርታ ተቀርጾ ወደ ሥራ ተገብቷል። በዚህም በዘርፉ የነበሩ መዋቅራዊ ችግሮችን በመለየት በምርትና ምርታማነት እንዲሁም በገበያ አድማስ ማስፋት ላይ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ ምርታማነታቸው ዝቅተኛ የነበሩ ያረጁ የቡና ተክሎችን በመጎንደል የማሳ ላይ ምርታማነትን የማሳደግ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል፡፡ በሀገር አቀፉ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ታግዞ አዳዲስ የቡና ችግኞች በስፋት መተከላቸውን ጠቁመዋል። በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን የምርት መጠን ብቻ ሳይሆን ጥራት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ቡናው በከፍተኛ ጥራት እንዲመረት ጥብቅ ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ምርታማነትን ከማሳደግ ጎን ለጎን የግብይት ሰንሰለቱን ማሳጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ሆኖ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም ለውጥ እየመጣ ይገኛል ብለዋል፡፡ ቀደም ሲል የነበረውን የተንዛዛ የገበያ ሥርዓት በፖሊሲ ማሳጠር በመቻሉ ይባክን የነበረውን የምርት መጠን መቀነስና በጥራት ላይ ይፈጠሩ የነበሩ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን ማስቀረት መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ ካላት የቡና አቅም አንጻር የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ እሴት ጨምሮ ለገበያ የማቅረብ ሥራ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ቀደም ሲል እሴት የተጨመረበት ቡና በምን ዓይነት የጥራት ደረጃና ሁኔታ ወደ ውጭ መላክ እንዳለበት የሚወስኑ ግልጽ መመሪያዎች ባለመኖራቸው ዘርፉ ሳይነቃቃ መቆየቱን አስረድተዋል። ይህንን ክፍተት በመሙላት ምቹ ሁኔታዎችን የሚፈጥር አዲስ መመሪያ ጸድቆ ወደ ሥራ መገባቱን ጠቁመው አዲሱ መመሪያ በሀገር ውስጥ የተቆላና የተፈጨ ቡናን በውጭ ምንዛሬ የመሸጥ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡ በዚህም በርካታ የቡና ቆይ ኩባንያዎች ምርቶቻቸውን በኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በትላልቅ ሆቴሎችና በቱሪስት መዳረሻዎች በውጭ ምንዛሬ መሸጥ መጀመራቸውን ጠቁመዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency  

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት ነዋሪዎች መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Jan 9, 2026 121
ሮቤ ፤ጥር 1/2018 (ኢዜአ):-በኦሮሚያ ክልል ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በባሌ ዞን የሀረና ቡሉቅ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። የዞኑ አስተዳደር በበኩሉ በ189 ቀበሌዎች የተዋቀረው አደረጃጀት ለነዋሪዎች አገልግሎት በቅርበት ለመስጠት ከማስቻሉ ባለፈ ጊዜና ወጪን በመቆጠብ በልማት ሥራዎች ላይ እንዲያተኩሩ ማድረጉን ገልጿል። አዲሱን የቀበሌ አደረጃጀት በማስመልከት አስተያየታቸውን ከሰጡ የሀረና ቡሉቅ የቁምቢ ቀበሌ ነዋሪዎች መካከል አቶ ሀሰን አህመድ እንዳሉት፣ አደረጃጀቱ ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎቶች በቅርበት ለማግኘት አስችሏቸዋል። ከዚህ በፊት መንግስታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደ ወረዳና ከተማ አስተዳደር የሚያደርጉት ምልልስ ጊዜና ድካም እንደነበረው አስታውሰው "አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት ይህንን በማቃለል ተጠቃሚ አድርጎናል" ብለዋል።   ሌላኛው ተገልጋይ አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው እንዳሉት የቀበሌ አደረጃጀቱ የህዝብን የልማት ተሳትፎ በማሳደግ ከዚህ በፊት የነበሩት የመሰረተ ልማት ችግሮች በህብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲፈቱ ዕድል ፈጥሯል። በአጭር ጊዜ ውስጥ ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከተከናወኑ የልማት ሥራዎች መካከል ድልድይና ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን ለአብነት ጠቅሰዋል። የሀረና ቡሉቅ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ሀሰን በበኩላቸው አዲሱ አደረጃጀት የወረዳውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በቅርበት ለመመለስ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። የባሌ ዞን አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ብርሃኑ አርፋሳ በበኩላቸው በዞኑ የሚገኙ 189 ቀበሌዎች በአዲሱ አደረጃጀት ተዋቅረው ወደ ሥራ መግባታቸውን ተናግሯል። በቀበሌ አደረጃጀቶችም አመራሮች ተመድበው ህብረተሰቡን በቅርበት እንዲያገለግሉ መደረጉን ገልጸዋል። እንደ አቶ ብርሀኑ ገለጻ በአዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት እየተሰጠ ያለው የህዝብ አገልግሎት ከዚህ በፊት ወደ ዞንና ወረዳዎች በተደጋጋሚ ይመጡ የነበሩ ቅሬታዎችን እየቀነሰና የህዝብ እርካታን እየጨመረ መጥቷል። በቀበሌዎቹ የተመደቡ አመራሮችና በለሙያዎች ህብረተሰቡን በተሻለ እንዲያገለግሉ የአቅም ግንባታ ሥልጠናና የድጋፍና ክትትል ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በቅርበት ለመፍታት አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት ተግባራዊ መደረጉ ይታወሳል። አደረጃጀቱ ህዝቡ በልማት ተጠቃሚ እንዲሆንና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎቹም በህዝብ ተሳትፎ መፍትሄ እንዲያገኙ ያለመ መሆኑ እንዲሁ።  
ኢትዮጵያ እና ቻይና በዘርፈ-ብዙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ ለማጠናከር ተወያዩ
Jan 8, 2026 151
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ በርካታ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ አጠናክረው ማስቀጠል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ተቀብዬ በጽናት በሚጓዘው የኢትዮጵያ እና ቻይና የመንግሥት እና ሕዝብ ግንኙነት ላይ ተነጋግረናል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ   ኢትዮጵያ እና ቻይና ለአስርት ዓመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። ይኽ ግንኙነት በቅርቡ ወደ በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የስትራቴጂክ ትብብር ማደጉንም አስታውቀዋል።   በተለያዩ የልማት ትብብር ርዕሰ ጉዳዮችን ለማከናወን ያለንን ጽኑ አቋም በማስቀጠል ላይ ውይይት አድርገናልም ነው ያሉት።   በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።  
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
Jan 6, 2026 341
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም መሰረት፦ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የማዳበሪያ ምርት ፈቃድ እና የፖታሽ ማዕድን ምርት ፈቃድ ረቂቅ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ለምክር ቤቱ የቀረቡት ሁለት ረቂቅ ስምምነቶች የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር፣ ሀገራችን ለማዳበሪያ ግዥ የምታወጣውን ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ ለማስቀረት እና ለሀገራችን አርሶ አደሮች ወቅቱን የጠበቀ የማዳበሪያ ስርጭት እንዲኖር ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውና ከአካባቢ ጥበቃና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት አንጻርም የመንግስትን የፖሊሲ አቅጣጫ የተከተሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ የማዕድን ሚኒስቴር ስምምነቶቹን እንዲፈራረምና ወደ ስራ እንዲገቡ ምክርቤቱ በሙሉ ድምጽ ይሁንታ ሰጥቷል፡፡   2. በመቀጠል የቤት ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ምከር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ ባለፉት አመታት በቂ የቤት አቅርቦት እንዲኖር የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም አሁንም የቤት አቅርቦትና ፍላጎት የተጣጣመ አይደለም፡፡ በመሆኑም በከተማና በገጠርለሚኖሩ ለሁሉም ዜጎች አቅምን ያገናዘበ፣ ተደራሽ እና በቂ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችል የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው ከኮሪያ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ ጋር በተደረገው የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት ላይ ነው፡፡ የብድር ስምምነቱ ለህከምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፕሮጄክት ምዕራፍ 2 ማስፈፀሚያ የሚውል 30,000,000 /ሰላሳ ሚሊዮን/የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኝ ሲሆን የሀከምና መሳሪያዎችን ችግር የሚፈታ፣ ዝቅተኛ ወለድ 0.01% የሚከፈልበት እና የከ5 አመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምከር ቤቱም ብድሩ ከሀገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋርየሚጣጣም መሆኑን በማረጋገጥ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡   4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው የተለያዩ አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ከፍያን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ተቋሙ ለተገልጋዮች ጥራትና ተዓማኒነት ያላቸው አገልግሎቶች ለመስጠት የሚያወጣቸውን ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ ወጪዎች የአገልግሎቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ ከሆነው የህብረተሰብ ክፍል ተመጣጣኝ ከፍያ በማስከፈል እንዲሸፍን ለማድረግ እንዲያስችለው ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምከር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይበሰፊው ከተወያየበት በኋላ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ደምጽ ወስኗል፡፡ 5. እንዲሁም የኅብረት ሥራ ማህበራት ማሻሻያ አዋጅ ምክር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 985/2009 ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ከተቀመጡ አቅጣጫዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማድረግ አዋጁን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 6. በማስከተልም የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቷል፡፡በአየር ትራንስፖርት ደህንነት፡ አስተማማኝነትና ቅልጥፍና ላይ የሚስተዋሉ የደህንነት ስጋቶችን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል አሰራር ለመተግበርየአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅ ቁጥር 432/1997ን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 7. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት ደንቦች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው የመሶብ አገልግሎትን ለማቋቋም የወጣው ደንብ ተገልጋዮች የመንግስት አገልግሎት ለማግኘት የሚያባከኑትን ጊዜ፣ ወጭ እና ጉልበት በመቆጠብ የተገልጋይ እርካታን የሚጨምርየአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ለመተግበር እንዲያስችል የቀረበ ሲሆን ሁለተኛው የኢትዮጵያ የብቃትና ሥራ አመራርኢንስቲትዩት አደረጃጀት፣ ሥልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣው ደንብ ተቋሙ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባርና ሃላፊነት ለመወጣት እንዲያስችለው ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ምክር ቤቱም በሁለቱም ደንቦች ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡   8. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው የሁሉን አቀፍ የተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠን፣ ምንጭ እና አስተዳደርን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ደንቡ በኢትዮጵያ የኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 148/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ (3) መሰረት የተቋቋመው የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሁሉን አቀፍ ተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠንና ምንጭ እንዲሁም ፈንዱ ስለሚተዳደርበት ሁኔታ ለመወሰን ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 9. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲዊ ሪፐብሊክ የስፖርት ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የስፖርት ፖሊሲ የማህበረሰቡን የስፖርት ተሳትፎ ከማረጋገጥ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርአት ከመዘርጋት፣ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋት የአበረታች ቅመሞችና ዘዴዎች ከመከላከል እና ስፖርትን ለማህበራዊ ልማት ከመጠቀም አንጻር ከፍተቶች የነበሩበት በመሆኑ ፖሊሲውን ለማሻሻል ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡   10. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የስፖርት ዘርፍ ካለው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲሁም አስተዳደራዊ ውስብስብነት አንጻር ዘርፉን በአግባቡ ለመምራት ዘመናዊ፣ አሳታፊና አካታች የሆነ የህግ ማዕቀፍና አስተዳደራዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡  
ሀገራዊ ምክክር፣ የዲሞክራሲ ባህልና የተቋማት ግንባታ ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ናቸው
Jan 6, 2026 182
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ምክክር፣ የዲሞክራሲ ባህልና የተቋማት ግንባታ ሥራዎች ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ወሳኝ መሰረት መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያን ችግሮች በመፍታት በተደመረ አቅም ሀገርን ለማበልፀግ ምሁራን ሀሳብ ከማመንጨትና ችግር ፈች ጥናት ከማድረግ ጀምሮ በተግባር ለውጥ የሚያመጣ ሥራን ሊከውኑ እንደሚገባም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን በማስመልከት “የምሁራን ሚና ለሀገር ብልፅግና” በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፖለቲካ ልዩነቶችን እንዴት ነው መፍታት የሚቻለው በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፥ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ልዩነቶችን መፍታት የቁርጠኝነትና የአቋም ጉዳይ መሆን አለበት ብለዋል። በየአካባቢው ያሉ የጽንፍ እሳቤዎች ኢትዮጵያን አንድ እርምጃ ወደ ፊት እንደማይወስዱ በማንሳት፥ ኢትዮጵያ የጋራችን ናት በሚል እሳቤ አምነን ከሠራን ወደተሻለ ምዕራፍ እንሻገራለን ነው ያሉት። ታሪክን በሚዛን፣ ዛሬን በትጋት፣ ነገን በተስፋ ነው የምንመለከተው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለሁሉም ህብረተሰብ እኩል እድል መስጠት እንደሚገባ ጠቅሰዋል። ጠንካራ ሀገራዊ አንድነት መፍጠር የሚቻለው የወል ትርክት በመገንባት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አንስተዋል።
የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለናል - የቀድሞ ታጣቂዎች
Jan 5, 2026 295
ጎንደር፤ ታህሳስ 27/2018(ኢዜአ)፦ የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለናል ሲሉ በአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በክልሉ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን ጥሪ በመቀበል የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን ለመንግስት በማስረከብ በጠዳ የስልጠና ማእከል የተሀድሶ ስልጠና ጀምረዋል።   በስልጠና ላይ ካሉት የቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው አስቻለው እሸቴ፣ አስቻለው ዳርጌ እና አንዳርጌ ሲሳይ፤ የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን መጥተናል ብለዋል። በክልሉ የውክልና ጦርነት ተልእኮ ፈፃሚ በመሆን ሰላምን ማናጋትና ህዝብን መጉዳት ታጋይነት ሳይሆን ባንዳነት መሆኑን ያነሱት ሰልጣኞቹ የነበርንበት መንገድ ፍፁም ስህተት መሆኑን ተገንዝበናል ሲሉ ተናግረዋል።   ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል አስቻለው እሸቴ፤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን ከጥፋት መንገድ ወጥተን መጥተናል፤ የበደልነውን ህዝብም በልማት ለመካስ ተዘጋጅተናል ብሏል። በክልሉ የተሳሳተ መንገድ ላይ የነበሩ ወጣቶች እየተመለሱ መሆኑን አንስቶ እርሱና ጓደኞቹም ይህንኑ እድል በመጠቀም መምጣታቸውን ተናግሯል። በመሆኑም ሌሎችም ጊዜ ሳያባክኑ ትጥቃቸውን በማስረከብ ለሰላማዊ ህይወት ተዘጋጅተው እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። ሌላኛው የቀድሞ ታጣቂ አስቻለው ዳርጌ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ሰርቶ ለመለወጥና የሰላም አምባሳደር በመሆን ህዝብን ለማገልገል መምጣቱን ተናግሯል።   የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የጥፋት መሳሪያ መሆን ከባንዳነት ውጭ ሌላ ትርጉም የሌለው መሆኑን አንስቶ፤ በጥፋቱ በመፀፀት ህዝብን በልማት ለመካስ መምጣቱን ገልጿል።   በመሆኑም የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ስልጠናውን ወስዶ ወደ ነበረበት ሰላማዊ ህይወት በመመለስ የበደለውን ህዝብ በልማት ለመካስ መዘጋጀቱን ገልጿል። የአማራ ክልል ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሃላፊ በሪሁን መንግስቴ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በየእለቱ እየመጡ መሆኑን ተናግረዋል።   በመሆኑም የቀድሞ ታጣቂዎቹን በመቀበልና የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት መልሰው እንዲቋቋሙ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ እየመጣ ላለው ሰላም የመንግስት ቁርጠኝነት እንዳለ ሆኖ በተለይም የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አጠቃላይ የህዝቡ ድምር ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።  
ፖለቲካ
አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት ነዋሪዎች መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Jan 9, 2026 121
ሮቤ ፤ጥር 1/2018 (ኢዜአ):-በኦሮሚያ ክልል ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በባሌ ዞን የሀረና ቡሉቅ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ። የዞኑ አስተዳደር በበኩሉ በ189 ቀበሌዎች የተዋቀረው አደረጃጀት ለነዋሪዎች አገልግሎት በቅርበት ለመስጠት ከማስቻሉ ባለፈ ጊዜና ወጪን በመቆጠብ በልማት ሥራዎች ላይ እንዲያተኩሩ ማድረጉን ገልጿል። አዲሱን የቀበሌ አደረጃጀት በማስመልከት አስተያየታቸውን ከሰጡ የሀረና ቡሉቅ የቁምቢ ቀበሌ ነዋሪዎች መካከል አቶ ሀሰን አህመድ እንዳሉት፣ አደረጃጀቱ ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎቶች በቅርበት ለማግኘት አስችሏቸዋል። ከዚህ በፊት መንግስታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደ ወረዳና ከተማ አስተዳደር የሚያደርጉት ምልልስ ጊዜና ድካም እንደነበረው አስታውሰው "አዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት ይህንን በማቃለል ተጠቃሚ አድርጎናል" ብለዋል።   ሌላኛው ተገልጋይ አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው እንዳሉት የቀበሌ አደረጃጀቱ የህዝብን የልማት ተሳትፎ በማሳደግ ከዚህ በፊት የነበሩት የመሰረተ ልማት ችግሮች በህብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲፈቱ ዕድል ፈጥሯል። በአጭር ጊዜ ውስጥ ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከተከናወኑ የልማት ሥራዎች መካከል ድልድይና ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን ለአብነት ጠቅሰዋል። የሀረና ቡሉቅ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ሀሰን በበኩላቸው አዲሱ አደረጃጀት የወረዳውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በቅርበት ለመመለስ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል። የባሌ ዞን አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ብርሃኑ አርፋሳ በበኩላቸው በዞኑ የሚገኙ 189 ቀበሌዎች በአዲሱ አደረጃጀት ተዋቅረው ወደ ሥራ መግባታቸውን ተናግሯል። በቀበሌ አደረጃጀቶችም አመራሮች ተመድበው ህብረተሰቡን በቅርበት እንዲያገለግሉ መደረጉን ገልጸዋል። እንደ አቶ ብርሀኑ ገለጻ በአዲሱ የቀበሌ አደረጃጀት እየተሰጠ ያለው የህዝብ አገልግሎት ከዚህ በፊት ወደ ዞንና ወረዳዎች በተደጋጋሚ ይመጡ የነበሩ ቅሬታዎችን እየቀነሰና የህዝብ እርካታን እየጨመረ መጥቷል። በቀበሌዎቹ የተመደቡ አመራሮችና በለሙያዎች ህብረተሰቡን በተሻለ እንዲያገለግሉ የአቅም ግንባታ ሥልጠናና የድጋፍና ክትትል ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በቅርበት ለመፍታት አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት ተግባራዊ መደረጉ ይታወሳል። አደረጃጀቱ ህዝቡ በልማት ተጠቃሚ እንዲሆንና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎቹም በህዝብ ተሳትፎ መፍትሄ እንዲያገኙ ያለመ መሆኑ እንዲሁ።  
ኢትዮጵያ እና ቻይና በዘርፈ-ብዙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ ለማጠናከር ተወያዩ
Jan 8, 2026 151
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ በርካታ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸውን በይበልጥ አጠናክረው ማስቀጠል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን ተቀብዬ በጽናት በሚጓዘው የኢትዮጵያ እና ቻይና የመንግሥት እና ሕዝብ ግንኙነት ላይ ተነጋግረናል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ይን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀበሉ   ኢትዮጵያ እና ቻይና ለአስርት ዓመታት የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸውም ገልጸዋል። ይኽ ግንኙነት በቅርቡ ወደ በሁኔታዎች የማይለዋወጥ የስትራቴጂክ ትብብር ማደጉንም አስታውቀዋል።   በተለያዩ የልማት ትብብር ርዕሰ ጉዳዮችን ለማከናወን ያለንን ጽኑ አቋም በማስቀጠል ላይ ውይይት አድርገናልም ነው ያሉት።   በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።  
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
Jan 6, 2026 341
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም መሰረት፦ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የማዳበሪያ ምርት ፈቃድ እና የፖታሽ ማዕድን ምርት ፈቃድ ረቂቅ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ለምክር ቤቱ የቀረቡት ሁለት ረቂቅ ስምምነቶች የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር፣ ሀገራችን ለማዳበሪያ ግዥ የምታወጣውን ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ ለማስቀረት እና ለሀገራችን አርሶ አደሮች ወቅቱን የጠበቀ የማዳበሪያ ስርጭት እንዲኖር ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውና ከአካባቢ ጥበቃና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት አንጻርም የመንግስትን የፖሊሲ አቅጣጫ የተከተሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ የማዕድን ሚኒስቴር ስምምነቶቹን እንዲፈራረምና ወደ ስራ እንዲገቡ ምክርቤቱ በሙሉ ድምጽ ይሁንታ ሰጥቷል፡፡   2. በመቀጠል የቤት ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ምከር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ ባለፉት አመታት በቂ የቤት አቅርቦት እንዲኖር የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም አሁንም የቤት አቅርቦትና ፍላጎት የተጣጣመ አይደለም፡፡ በመሆኑም በከተማና በገጠርለሚኖሩ ለሁሉም ዜጎች አቅምን ያገናዘበ፣ ተደራሽ እና በቂ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችል የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው ከኮሪያ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ ጋር በተደረገው የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት ላይ ነው፡፡ የብድር ስምምነቱ ለህከምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፕሮጄክት ምዕራፍ 2 ማስፈፀሚያ የሚውል 30,000,000 /ሰላሳ ሚሊዮን/የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኝ ሲሆን የሀከምና መሳሪያዎችን ችግር የሚፈታ፣ ዝቅተኛ ወለድ 0.01% የሚከፈልበት እና የከ5 አመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምከር ቤቱም ብድሩ ከሀገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋርየሚጣጣም መሆኑን በማረጋገጥ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡   4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው የተለያዩ አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ከፍያን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ተቋሙ ለተገልጋዮች ጥራትና ተዓማኒነት ያላቸው አገልግሎቶች ለመስጠት የሚያወጣቸውን ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ ወጪዎች የአገልግሎቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ ከሆነው የህብረተሰብ ክፍል ተመጣጣኝ ከፍያ በማስከፈል እንዲሸፍን ለማድረግ እንዲያስችለው ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምከር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይበሰፊው ከተወያየበት በኋላ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ደምጽ ወስኗል፡፡ 5. እንዲሁም የኅብረት ሥራ ማህበራት ማሻሻያ አዋጅ ምክር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 985/2009 ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ከተቀመጡ አቅጣጫዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማድረግ አዋጁን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 6. በማስከተልም የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቷል፡፡በአየር ትራንስፖርት ደህንነት፡ አስተማማኝነትና ቅልጥፍና ላይ የሚስተዋሉ የደህንነት ስጋቶችን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል አሰራር ለመተግበርየአቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅ ቁጥር 432/1997ን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማሻሻያ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 7. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት ደንቦች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው የመሶብ አገልግሎትን ለማቋቋም የወጣው ደንብ ተገልጋዮች የመንግስት አገልግሎት ለማግኘት የሚያባከኑትን ጊዜ፣ ወጭ እና ጉልበት በመቆጠብ የተገልጋይ እርካታን የሚጨምርየአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ለመተግበር እንዲያስችል የቀረበ ሲሆን ሁለተኛው የኢትዮጵያ የብቃትና ሥራ አመራርኢንስቲትዩት አደረጃጀት፣ ሥልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣው ደንብ ተቋሙ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባርና ሃላፊነት ለመወጣት እንዲያስችለው ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ምክር ቤቱም በሁለቱም ደንቦች ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡   8. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው የሁሉን አቀፍ የተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠን፣ ምንጭ እና አስተዳደርን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ደንቡ በኢትዮጵያ የኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 148/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ (3) መሰረት የተቋቋመው የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሁሉን አቀፍ ተደራሽነት ፈንድ የገቢ መጠንና ምንጭ እንዲሁም ፈንዱ ስለሚተዳደርበት ሁኔታ ለመወሰን ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 9. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲዊ ሪፐብሊክ የስፖርት ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ በስራ ላይ ያለው የስፖርት ፖሊሲ የማህበረሰቡን የስፖርት ተሳትፎ ከማረጋገጥ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርአት ከመዘርጋት፣ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋት የአበረታች ቅመሞችና ዘዴዎች ከመከላከል እና ስፖርትን ለማህበራዊ ልማት ከመጠቀም አንጻር ከፍተቶች የነበሩበት በመሆኑ ፖሊሲውን ለማሻሻል ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡   10. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የስፖርት ዘርፍ ካለው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲሁም አስተዳደራዊ ውስብስብነት አንጻር ዘርፉን በአግባቡ ለመምራት ዘመናዊ፣ አሳታፊና አካታች የሆነ የህግ ማዕቀፍና አስተዳደራዊ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡  
ሀገራዊ ምክክር፣ የዲሞክራሲ ባህልና የተቋማት ግንባታ ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ናቸው
Jan 6, 2026 182
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ምክክር፣ የዲሞክራሲ ባህልና የተቋማት ግንባታ ሥራዎች ለሁሉም የምትመች ሀገር ለመገንባት ወሳኝ መሰረት መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያን ችግሮች በመፍታት በተደመረ አቅም ሀገርን ለማበልፀግ ምሁራን ሀሳብ ከማመንጨትና ችግር ፈች ጥናት ከማድረግ ጀምሮ በተግባር ለውጥ የሚያመጣ ሥራን ሊከውኑ እንደሚገባም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን በማስመልከት “የምሁራን ሚና ለሀገር ብልፅግና” በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፖለቲካ ልዩነቶችን እንዴት ነው መፍታት የሚቻለው በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፥ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ልዩነቶችን መፍታት የቁርጠኝነትና የአቋም ጉዳይ መሆን አለበት ብለዋል። በየአካባቢው ያሉ የጽንፍ እሳቤዎች ኢትዮጵያን አንድ እርምጃ ወደ ፊት እንደማይወስዱ በማንሳት፥ ኢትዮጵያ የጋራችን ናት በሚል እሳቤ አምነን ከሠራን ወደተሻለ ምዕራፍ እንሻገራለን ነው ያሉት። ታሪክን በሚዛን፣ ዛሬን በትጋት፣ ነገን በተስፋ ነው የምንመለከተው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ለሁሉም ህብረተሰብ እኩል እድል መስጠት እንደሚገባ ጠቅሰዋል። ጠንካራ ሀገራዊ አንድነት መፍጠር የሚቻለው የወል ትርክት በመገንባት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አንስተዋል።
የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለናል - የቀድሞ ታጣቂዎች
Jan 5, 2026 295
ጎንደር፤ ታህሳስ 27/2018(ኢዜአ)፦ የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለናል ሲሉ በአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በክልሉ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን ጥሪ በመቀበል የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን ለመንግስት በማስረከብ በጠዳ የስልጠና ማእከል የተሀድሶ ስልጠና ጀምረዋል።   በስልጠና ላይ ካሉት የቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው አስቻለው እሸቴ፣ አስቻለው ዳርጌ እና አንዳርጌ ሲሳይ፤ የነበርንበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በአግባቡ በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን መጥተናል ብለዋል። በክልሉ የውክልና ጦርነት ተልእኮ ፈፃሚ በመሆን ሰላምን ማናጋትና ህዝብን መጉዳት ታጋይነት ሳይሆን ባንዳነት መሆኑን ያነሱት ሰልጣኞቹ የነበርንበት መንገድ ፍፁም ስህተት መሆኑን ተገንዝበናል ሲሉ ተናግረዋል።   ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል አስቻለው እሸቴ፤ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለን ከጥፋት መንገድ ወጥተን መጥተናል፤ የበደልነውን ህዝብም በልማት ለመካስ ተዘጋጅተናል ብሏል። በክልሉ የተሳሳተ መንገድ ላይ የነበሩ ወጣቶች እየተመለሱ መሆኑን አንስቶ እርሱና ጓደኞቹም ይህንኑ እድል በመጠቀም መምጣታቸውን ተናግሯል። በመሆኑም ሌሎችም ጊዜ ሳያባክኑ ትጥቃቸውን በማስረከብ ለሰላማዊ ህይወት ተዘጋጅተው እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። ሌላኛው የቀድሞ ታጣቂ አስቻለው ዳርጌ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ሰርቶ ለመለወጥና የሰላም አምባሳደር በመሆን ህዝብን ለማገልገል መምጣቱን ተናግሯል።   የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የጥፋት መሳሪያ መሆን ከባንዳነት ውጭ ሌላ ትርጉም የሌለው መሆኑን አንስቶ፤ በጥፋቱ በመፀፀት ህዝብን በልማት ለመካስ መምጣቱን ገልጿል።   በመሆኑም የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል ስልጠናውን ወስዶ ወደ ነበረበት ሰላማዊ ህይወት በመመለስ የበደለውን ህዝብ በልማት ለመካስ መዘጋጀቱን ገልጿል። የአማራ ክልል ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሃላፊ በሪሁን መንግስቴ፤ የመንግስትን የሠላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በየእለቱ እየመጡ መሆኑን ተናግረዋል።   በመሆኑም የቀድሞ ታጣቂዎቹን በመቀበልና የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት መልሰው እንዲቋቋሙ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በክልሉ እየመጣ ላለው ሰላም የመንግስት ቁርጠኝነት እንዳለ ሆኖ በተለይም የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አጠቃላይ የህዝቡ ድምር ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።  
ማህበራዊ
በክልሉ በጤና ተቋማት ወቅቱን የተከተለ የዲጂታል አሰራርን በመተግበር የእናቶችን ጤና ለመጠበቅ ትኩረት ተደርጓል
Jan 9, 2026 49
ሰመራ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በጤና ተቋማት ወቅቱን የተከተለ የዲጂታል አሰራርን በመተግበር የእናቶችን ጤና ለመጠበቅ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለፀ። ቢሮው "ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለእናቶች ጤና" በሚል መሪ ሐሳብ ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ አንድ ወር በተለያዩ ኹነቶች የሚከበረውን የእናቶች ጤና ወርን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ዊቲካ ኖሬ በመግለጫቸው እንዳሉት የእናቶችን ጤና መጠበቅ ሲቻል የቤተሰብና የህብረተሰብ ጤና የተጠበቀና ጤናማ ትውልድ ማፍራት ያስችላል። በዚህም በቀጣይ በሚከናወኑ ኹነቶች ፈጠራና ክህሎትን በማሳደግ እንዲሁም በጤና ተቋማት የማዋለጃ ቁሳቁሶችን ማዘመንና ወቅቱን የተከተለ የዲጂታል አሰራር ላይ ትኩረት በማድረግ ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል። ዘላቂነት ያለው የገንዘብ ምንጮችን በማጎልበት በእናቶች ደህንነት እና ጤና ላይ ከአጋር አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራም አስረድተዋል። በተለይም አቅመ ደካማ እናቶችን በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ ከባለሃብቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር በመስራትና በአካባቢ ያለን ፀጋ በመጠቀም የገንዘብ ማግኛ አማራጮችን የማስፋት ስራም ይሰራል ብለዋል። በዚሁ በእናቶች ወር ከሚከናወኑት የንቅናቄ ስራዎች መካከል በተለይም የአርብቶ አደሩ አካባቢ እናቶች በጤና ተቋማት ብቻ እንዲወልዱና የህክምና ክትትላቸውን እንዲያደርጉ ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እንደሚሰራም ገልጸዋል። በተጨማሪም ከተንቀሳቃሽነት የኑሮ ዘይቤ ይልቅ በቋሚ ስፍራ እንዲኖሩ የሚያስችሉ ተግባራትም በትኩረት ይከናወናሉ ብለዋል። በክልሉ የጤና ክትትል የሚደረግላትና ደህንነቷ የተጠበቀ እናት እንድትኖር የሚከናወኑ ተግባራት እንዲጠናከሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል። በቅርቡ የተከፈተው የዱብቲ የእናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከልን እንደ አብነት ያነሱት ምክትል ሃላፊው፤ መሰል የጤና ተቋማትን ማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት መሆኑን ገልፀዋል። በእናቶች ጤንነትና ደህንነት ላይ የሚሰሩ ስራዎች መመዝገብ፣ መከታተልና ማስቀመጥ ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚከናወንም ነው ያስረዱት።      
በኢትዮጵያ የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤት አስገኝተዋል
Jan 9, 2026 77
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤት ማምጣታቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ። ሚኒስትሯ በጥር ወር የሚከበረውን "የጤናማ እናትነት ወር" አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ባለፉት ዓመታት ከወሊድ ጋር ተያይዞ የሚከሰት የጤና ችግርና ሞትን ለመቀነስ በተደረገው ርብርብ በጤና ተቋማት የሚወልዱ እናቶች ቁጥር መጨመሩን ተናግረዋል፡፡ በጤና ጣቢያዎች የቀዶ ሕክምና አገልግሎት መጀመሩ ለውጥ ማምጣቱንም ጠቅሰው የጤና ተቋማት ተደራሽነት መስፋት የቅድመ ወሊድ ክትትልን ማሳደጉንም ነው የገለጹት፡፡ ከወሊድ በኋላ የሚከሰት የደም መፍሰስን በመከላከል በኩል የበጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች ሚና እና ቁጥር ማደጉንም ተናግረዋል፡፡ እስካሁን የተገኙ ውጤቶች አበረታች መሆናቸውን ጠቁመው በቀጣይም የተሻሉ ውጤታማ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል፡፡ ለዚህም ፈጠራ እና ዘላቂ ፋይናንስ ወሳኝ መሆናቸውን ጠቅሰው የዲጂታል ጤና መረጃን ተደራሽ ማድረግ፣ የሕክምና ግብዓቶችን ማሟላትና የቀዶ ሕክምና አገልግሎትን ማስፋት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ጤናማ እናትነት አንዲት ሴት በእርግዝና፣ በወሊድና በድህረ ወሊድ ወቅት የሚኖራት ሁለንተናዊ ጤንነት ነው። የዘንድሮው የጤናማ እናትነት ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ39ኛ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ ''ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች ይከበራል።
ለጥምቀት በዓል ወደ ጎንደር ከተማ የሚመጡ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ፓርኩን እንዲጎበኙ ዝግጅት ተደርጓል
Jan 9, 2026 68
ጎንደር፤ ጥር 1/2018 (ኢዜአ)፡-የጥምቀት በዓልን ለማክበር ወደ ጎንደር ከተማ የሚመጡ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን እንዲጎበኙ ልዩ የጉብኝት ፓኬጅ መዘጋጀቱን የፓርኩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የፓርኩ ጽህፈት ቤት ተወካይ ሃላፊ አቶ ላቀው መልካሙ ለኢዜአ እንደገለጹት የጥምቀት በዓልን ለመታደም ወደ ጎንደር ከተማ የሚመጡ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ፓርኩን እንዲጎበኙ የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል፡፡ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ዋልያ፤ ቀይ ቀበሮና ጭላዳ ዝንጀሮን ጨምሮ ሌሎች ብርቅዬ የዱር እንስሳትና አዕዋፋት መገኛ ስፍራ በመሆኑ በጎብኚዎች ተመራጭ መሆኑን ገልጸዋል።   ይህን የሀገር ቅርስ ጥምቀትን ምክንያት በማድረግ ለማስጎብኘት መታቀዱን የገለጹት አቶ ላቀው፣ የጉብኝት ፓኬጁ ተራራ መውጣት፤ የእግር ጉዞዎች፤ ብርቅዬ የዱር አንስሳት የሚገኙባቸው ስፍራዎችን መጎብኘት እንደሚያካትት ተናግረዋል። የፓርኩን መሰረተ ልማቶች የመጠገንና የማስተካከል ሥራዎች መከናወናቸው ጠቁመው፣ ፓኬጁ መዘጋጀቱ የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም ያስችላል ብለዋል። ለቱሪስቶች ማረፊያ የሚያገለግሉ የካምፕና የድንኳን መጠለያ ቦታዎችን፣ የውሃ ተቋማትንና መጸዳጃ ቤቶችን በማዘጋጃት የተሟላ መስተንግዶ እንዲያገኙ የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ በአካባቢው በአስጎብኝነትና በምግብ አብሳይነት የተደራጁ ማህበራትን በቅድመ ዝግጅት ወቅት በቱሪስቶች መስተንግዶና አያያዝ ስልጠና መሰጠቱንም አስረድተዋል፡፡ የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን ቁጥርን ለማሳዳግ ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ ፓርኩን የማስተዋወቅ ሥራዎች በስፋት መከናወናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ላቀው ገለጻ ባለፉት ስድስት ወራት ፓርኩን የጎበኙ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ቁጥር 1ሺህ 400 መድረሱን ጠቁመው፣ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ600 እድገት አሳይቷል ብለዋል የደባርቅ የኢኮ ቱሪዝም ማህበራት ዩኒየን ሥራ አስኪያጅ ቄስ ሞገስ አየነው በበኩላቸው የፓርኩ የቱሪስት ፍሰት መጨመር በዩኒየኑ የታቀፉ አባላት ከቱሪዝም ገቢው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል፡፡ ስምንት ሺህ የሚደርሱ የዩኒየኑ አባላት በቅሎ በማከራየት፣ የጎብኚዎችን እቃ በመጫን፣ በማጀብና መንገድ በመምራት ቱሪስቶችን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ 412 ስኩየር ኪሎ ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን እንደ አውሮፓውያኑ የዘመን ቀመር በ1978 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም የተፈጥሮ ቅርስነት ተመዝግቧል፡፡  
የባህር ዳር ከተማ አካታች የኮሪደር ልማት የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው
Jan 9, 2026 72
ባሕር ዳር፤ ጥር 1/ 2018(ኢዜአ)፡- የባህር ዳር ከተማ አካታች የኮሪደር ልማት የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድግ መሆኑን የአማራ ክልል አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ገለጸ። የፌደሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ፍሬሰላም ዘገየ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማዋ የተገነባው የኮሪደር ልማት የአካል ጉዳተኞችን የልማትና ማህበራዊ ተሳትፎ የሚያሳድግ ነው። የኮሪደር ልማቱ የእግረኛ፣ የብስክሌትና የተሽከርካሪ መንገዶችን ለይቶ በመከናወኑ ቀደም ሲል ለአካል ጉዳተኞች እንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበረውን ሁኔታ እንደሚያቃልል ጠቁመዋል።   በተለይም ቀደም ባለው ጊዜ የእግረኛና የተሽከርካሪ መንገድ በተገቢው ባለመለየቱና፣ ያለቦታው የሚተከሉ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች እንዲሁም ያልተዘጉ ቦዮች ዓይነስውራንና በዊልቸር የሚንቀሳቀሱ አካል ጉዳተኞችን ለጉዳት ሲያጋልጡ እንደነበር አስታውስዋል። በፌዴሬሽኑ የሴት አካል ጉዳተኞች ዘርፍ አስተባባሪ ወይዘሮ ባንቻምላክ አቤ በበኩላቸው፤ የኮሪደር ልማቱ የአካል ጉዳተኞችን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።   ልማቱ ዐይነ ስውራንና ዊልቼር ተጠቃሚዎች በነጻነት ተንቀሳቅሰው ህይወታቸውን እንዲመሩ እድል የፈጠረ መሆኑንም አንስተዋል። የከተማዋ የኮሪደር ልማት የአካል ጉዳተኞችን የልማት ተሳትፎን እንደሚያጠናክር ያነሱት ደግሞ የአማራ ክልል ዐይነ ስውራን ማህበር ሰብሳቢና የፌዴሬሽኑ የቦርድ አባል አቶ ክርስቲያን ይበልጣል ናቸው።   ከዚህ በፊት የሚገነቡት መሰረተ ልማት ስራዎች አካል ጉዳቶችን ታሳቢ ባለማድረጋቸው አካል ጉዳተኞች ከተሽከርካሪ ጋር በመጋፋት ለአደጋ ይጋለጡ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህንን ችግር በማቃለል ከፍተኛ እገዛ ያደረገው የኮሪደር ልማትን በማጠናክር ወደ ሌሎች ከተሞች ማስፋት እንደሚገባም ጠቁመዋል። በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአማራ ክልል ከተሞችና መሰረተ ልማት ቢሮ አማካሪ አቶ ሽቤ ክንዴ፤ እንደገለጹት በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ሰው ተኮርና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያማከለ ነው ብለዋል።   መሰረተ ልማት ዝርጋታዎቹ የስማርት ሲቲን ፕላን ደረጃን ጠብቀው በመከናወኑ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆኑን ገልጸዋል። የከተማዋ መዋቅር ከተሞች ለስራ ፈጠራና ለማህበራዊ እንቅስቃሴዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ መሰረት የጣሉ ናቸው ብለዋል። የከተሞቹ አካታች የመሰረተ ልማት ግንባታ በተለይም በዊልቼር፣ በክራንች እና በሌሎች የአካል ድጋፍ የሚንቀሳቀሱ ወገኖች የልማት ተሳትፎን ለማሳደግ የማይተካ ድርሻ ያላቸው በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።
ኢኮኖሚ
በዞኑ ከ12 ሺህ 600 ቶን በላይ የማር ምርት ለገበያ ይቀርባል
Jan 9, 2026 26
ነቀምቴ ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ወለጋ ዞን በበጀት ዓመቱ 12 ሺህ 674 ቶን የማር ምርት ለገበያ እንደሚቀርብ የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት አስታወቀ። በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የልማት ኢንሼቲቭ ተቀርጾላቸው በአዲስ መልክ እየተሰራባቸው ካሉ የግብርና ስራዎች መካከል የማር ልማት አንዱ ነው። የምስራቅ ወለጋ ዞን ለማር ልማት አመቺ ከሚባሉት የክልሉ ዞኖች አንዱ ነው። በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የእንስሳት እንክብካቤና ልማት ክፍል ሃላፊ አቶ አዲሱ ዳቤ፣ በዞኑ የሚገኘውን ምቹ የአየር ሁኔታ እና የደን ሀብት በመጠቀም የማር ምርት መጠንን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።   በተያዘው በጀት ዓመትም 12 ሺህ 674 ቶን ለገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አንስተው በእስካሁኑ እንቅስቃሴ ከ8 ሺህ ቶን በላይ የማር ምርት ለገበያ መቅረቡን ገልጸዋል። በዘርፉ የተያዘው እቅድ እንዲሳካም ዘመናዊ ቀፎዎች ለአርሶ አደሩ በስፋት እንዲቀርቡ መደረጉንም ነው የገለጹት። በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ 2 ሺህ 500 ዘመናዊ ቀፎዎች ለአርሶ አደሩ የቀረበ ሲሆን በድምሩ በ38 ሺህ 147 ተሸጋጋሪ ቀፎ እና በ84 ሺህ 961 ባህላዊ ቀፎዎች የንብ ማነብ ስራው እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። በዞኑ ከ26 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በንብ ማነብ ስራ መሰማራታቸውን ገልጸው አብዛኞቹ ማር አምራቾች በዞኑ ዲጋ ወረዳ እንደሚገኙ አመልክተዋል። የዲጋ ወረዳ የግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ይስሐቅ አዲሱ፣ በወረዳው በ22 ሺህ 500 ዘመናዊ ቀፎ የንብ ማነብ ስራ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።   በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 820 ቶን ማር ተመርቶ ለገበያ መቅረቡን አንስተው በወረዳው 13 ሺህ 760 አርሶ አደሮች በንብ ማነብ ስራው ተሰማርተው ይገኛሉ ብለዋል። በማህበር ከተደራጁ ማር አምራች የወረዳው አርሶ አደሮች መካከል ማሞ ኡመታ እና ጓደኞቻቸው ሰባት ሆነው በ50 ዘመናዊ ቀፎ የንብ ማነብ ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ። ባለፈው ዓመት 120 ኪሎ ግራም ለገበያ ማቅረባቸውን ተናግረው በዚህ ዓመት 200 ኪሎ ግራም ማር ለገበያ ለማቅረብ እየተዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው የወረዳው ነዋሪ አቶ ብርሃኑ ሂንኮ፤ ባላቸው ሰባት ዘመናዊ ቀፎ የንብ ማነብ ስራ እያከናወኑ ሲሆን ዘንድሮም 40 ኪሎ ግራም ማር ለገበያ ማቅረባቸውን ተናግረዋል።
በንጋት ሰው ሰራሽ ሐይቅ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚዎች ምቹ የልማት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቷል
Jan 9, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የንጋት ሰው ሰራሽ ሐይቅ ላይ በቱሪዝም ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚዎች ምቹ የልማት ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር ገለጸ። የለውጡ መንግስት ቱሪዝምን ከአምስቱ ግንባር ቀደም የኢኮኖሚ ምሰሶዎች መካከል በማድረግ ለቅርስ ጥበቃ፣ ዕድሳትና ለአዳዲስ የመዳረሻ ልማት የሰጠው ትኩረት ዘርፉ እንዲያንሰራራ አስችሏል። የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በርካታ ቀልብን የሚስቡ ታሪካዊ፣ ኃይማኖታዊ፣ ባህላዊና ተፈጥሯዊ የመስህብ ዕምቅ ጸጋዎችን የታደለች ሀገር ናት።   ከቅርብ ዓመታት ወዲህም የኢትዮጵያን ዕምቅ የመስህብ ጸጋዎች በመንከባከብና በማልማት የቱሪዝም ሃብት ወሳኝ የኢኮኖሚ አቅም እንዲሆን እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተገነቡ ማራኪ የመዳረሻ ሥፍራዎችም ለጎብኝዎች ምቹ ምኅዳርን በመፍጠር የቱሪዝም ተወዳዳሪነትን በእጅጉ እያሳደጉ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቱሪዝም፣ የዓሳ ሃብት ልማት፣ የውሃ ላይ ትራንስፖርትና መሰል የመስህብ መዳረሻ ኢንቨስትመንትን ማሳደግ የሚያስችል ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱንም አስረድተዋል። በሕዳሴ ግድብ የንጋት ሐይቅ እና ዙሪያውን ለማልማት የተዘጋጀው ፍኖተ ካርታ የግሉን ዘርፍ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ተሳትፎ የሚያሳድግ ዕድል መፍጠር እንደቻለ ገልጸዋል።   ለዚህም የግሉ ዘርፍ በንጋት ሐይቅ የቱሪዝም ልማት ኢንቨስትመንት ተሳትፎን ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት፣ ከፌደራልና ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መንግስት ጋር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በንጋት ሐይቅ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ለሚሳተፉ አልሚዎችም የግንባታ መሳሪያ፣ ተሽከርካሪ እና መሰል ቁሳቁሶች ከቀረጥ ነፃ አገልግሎት የሚያገኙበት ዕድል መመቻቸቱን አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በየዘርፉ ለሚዘጋጁ እቅዶች፣ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ትክክለኛ ግብዓት ያስገኛል
Jan 9, 2026 27
ሐረማያ፤ ጥር 1/2018(ኢዜአ)፦ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በየዘርፉ ለሚዘጋጁ እቅዶች፣ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ትክክለኛ ግብዓት እንደሚያስገኝ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ገለጸ። አገልግሎቱ ለሁለተኛ ዙር የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የአሰልጣኞች ስልጠና በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ባለሙያዎች በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እየሰጠ ነው። በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከፍተኛ የስታቲስቲክስ ባለሙያ እና በስልጠናው የቴክኒክ ዋና አስተባባሪ ሃይሌ ዓለሙ እንዳሉት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዘርፈ ብዙና የተለያዩ መረጃዎችን ይሰበስባል፤ ይተነትናል።   የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን ለሚያደርጉ ባለሙያዎችም የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው፤ በስልጠናው የኢኖሚ ድርጅቶች ትርጉም፣ ጽንሰ ሃሳብ፣ ዓላማና ሌሎች መረጃ ለመሰብሰብ የሚያገለግሉ ሃሳቦችን የሚገነዘቡበት መሆኑን ተናግረዋል። የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ዓላማም የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሃብት ደረጃ ለማወቅና ድርጅቶችን በዓይነት፣ በብዛትና በደረጃ ለመለየት እንዲሁም ለጥናትና ምርምር፣ ለፖሊሲ፣ ለስትራቴጂና እቅድ ዝግጅት ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች አሉት ብለዋል። በአገልግሎቱ የሐረር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ሙክታር ጀማል እንደገለጹት በቅርንጫፉ አስተባባሪነት ከሐረር፣ ድሬዳዋ፣ ጭሮ፣ ጎዴና ጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ለተውጣጡ 180 ሰዎች የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ተጀምሯል።   የአሰልጣኞች ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚቆይ ጠቁመው፤ ስልጠናው ጥራትና ወቅቱን የጠበቀ፣ ተገቢነትና ተአማኒነት ያለው መረጃ መሰብሰብ የሚያስችል ክህሎት እንዲያገኙና ሌሎችን እንዲያበቁ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።
በዞኑ ከ37 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ለምቷል
Jan 9, 2026 49
ደብረ ማርቆስ፤ጥር 1/2018(ኢዜአ)፡-በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ37 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ማልማት መቻሉን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ። በመምሪያው የመስኖ ልማት ቡድን መሪ አቶ ሃብታሙ አህመድ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ የመስኖ ልማቱን ምርታማነት በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ርብርብ እየተደረገ ነው። በበጀት ዓመቱም በ1ኛ ዙር ብቻ ከ41 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ከ37 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈን መቻሉን ገልጸዋል። በመስኖ ከለማው መሬትም ከ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ብለዋል። የበጋ መስኖ ልማት ስራው ከ120 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ9 ሺህ 700 በላይ የሞተር ፓምፕ እና ዘመናዊ የመስኖ ግንባታዎች ጥቅም ላይ መዋላቸውን አስረድተዋል። የመስኖ ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግም ከ84 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቁመዋል። በመስኖ የለሙ አትክልትና ሰብሎችን ከተባይ የመከላከልና የመንከባከብ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በዞኑ በመስኖ ልማት ስራው ከተሰማሩ አርሶ አደሮች መካከል የጎዛምን ወረዳ የመጣያ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መኩሪያው የስጋት እንዳሉት የዝናብ ወቅትን ብቻ ጠብቀው በማምረት ቤተሰባቸውን በተገቢው ማስተዳደር እንዳልቻሉ አስታውሰዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በመስኖ ልማት በመሰማራት በዓመት ሁለት ጊዜ በማምረት የቤተሰባቸውን የምግብ ዋስትና እንዳረጋገጡ ጠቁመዋል። በመስኖ ስንዴንና የጓሮ አትክልቶችን በማልማት በዓመት እስከ 90 ሺህ ብር ተጨማሪ ገቢ እንደሚያገኙም ተናግረዋል። የዚሁ ወረዳ የደሳ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ያለምወረቅ ምህረት በበኩላቸው ባለፈው ዓመት በመስኖ የጓሮ አትክልት በማልማት ከ30 ሺህ ብር በላይ ተጨማሪ ገቢ ማግኘታቸውን አውስተዋል። በያዝነው በጋ የምርት ማሳደጊያ ግብዓት በመጠቀማቸው ምርታማነታቸውን በማሳደግ ከ40 ሺህ ብር በላይ ገቢ ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል። በዞኑ ባለፈው ዓመት በ1ኛና 2ኛ ዙር በመስኖ ከለማው መሬት ላይ አራት ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት መገኘቱን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።  
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ለጉምሩክ አገልግሎት መቀላጠፍ ትልቅ ዕድል ይዞ መጥቷል
Jan 8, 2026 156
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ቀልጣፋ የጉምሩክ አገልግሎትን ለማጠናከር ትልቅ ዕድል ይዞ መምጣቱን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ዋነኛ ዓላማዎቹ ናቸው። የጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሙሉ ወርቅ ደረሰ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኮሚሽኑ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትግበራ ወቅት የንግድ እንቅስቃሴን የሚያሳልጡ፣ ኮንትሮባንድን ለመቆጣጠር የሚያስችሉና በአጠቃላይ የኮሚሽኑን ስራዎች የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎች ወደ ሥራ አስገብቷል። ቴክኖሎጂዎቹ ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን ክትትል ለማጠናከር፣ የሰው ንክኪና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል እንዲሁም ደንበኞች ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ደግሞ በጉምሩክ ዘርፍ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማዘመን እና ለማቀላጠፍ ትልቅ እድል ይዞ መምጣቱን ጠቅሰዋል። ስትራቴጂውን ስኬታማ ለማድረግ የተቋማት ቅንጅት እንደ ዋነኛ የድጋፍ ማዕቀፍ መሆኑን በማንሳት፥ ኮሚሽኑ የበከሉን ይወጣል ብለዋል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ አሰራር ተግባራዊ መደረጉን ገልጸው፤ በሂደት ላይም ያሉ ቴክኖሎጂዎች በቀጣይ ወደ ስራ ይገባሉ ብለዋል። ምክትል ኮሚሽነሯ እንደገለጹት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የጉምሩክ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የማድረግ ሰራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።  
የኢትዮጵያ ሳተላይቶች ያመነጯቸው መረጃዎች ጉልህ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አበርክተዋል 
Jan 8, 2026 94
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሳተላይቶች ያመነጯቸው መረጃዎች ጉልህ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማበርከታቸውን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ገለጸ። በሚቀጥለው ዓመትም ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ የመረጃ ሳተላይት ወደ ሕዋ ለማምጠቅ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል። የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን ሳተላይት ኢቲ-አር.ኤስ.ኤስ1 (ET-RSS1) እንዲሁም ሁለተኛው ኢቲ-ስማርት-አር.ኤስ.ኤስ (ET-SMART-RSS) የተሰኙ ሁለት የመረጃ ሳተላይቶችን ወደ ሕዋ ማምጠቋ ይታወሳል።   የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ቀደም ሲል ወደሕዋ የተላኩ ሁለት የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች የአገልግሎት ጊዜያቸውን አጠናቀዋል። የመሬት ምልከታ የመረጃ ሳተላይቶቹም በርካታ ቴክኖሎጂያዊና ሳይንሳዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን ማበርከታቸውን ተናግረዋል። በዚህም የምግብ ዋስትና፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በተፈጥሮ ሃብት አያያዝ የግብርና መስኮች፣ በከተማ ፕላንና መሠረተ ልማት፣ በሀገር ሉዓላዊነትና ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ጠቀሜታ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም በሚቀጥለው ታኅሳስ 2019 ዓ.ም በምስል ጥራትና የጊዜ ቆይታ አቅም ያላት ኢቲ-አር.ኤስ.ኤስ 2 (ET-RSS2) የተሰኘች ሳተላይት ወደ ሕዋ ለማምጠቅ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።   በቀጣይ የምትመጥቀው ኢቲ-አር.ኤስ.ኤስ 2 ሳተላይት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመታጠቅ በሕዋ ላይ የአምስት ዓመታት የጊዜ ቆይታ እንዲኖራት ታሳቢ መደረጉ ነው የተገለጸው። ከዚህ ቀደም ወደ ሕዋ ከተላኩ ሳተላይቶች የተገኘውን መረጃ የመቀበል፣ የመተንተን፣ የመቆጣጠርና የጥገና አቅም መፈጠሩን አስረድተዋል። ሦስተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ እየተደረገ የሚገኘው ጥረትም የኢትዮጵያን የሳተላይት ልማት አቅም በተግባር የሚያሳይ እንደሚሆን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረት እየጣለች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jan 6, 2026 151
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የፖሊሲ ማዕቀፍ እና መሰረተ ልማትን ጨምሮ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረት የሚጥሉ ስራዎችን እያከናወነች እንደምትገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በማስመልከት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሑፍ አቅርበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ ከምሁራን ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤ.አይ) በዓለም ደረጃ ያለው ተጽእኖ እና ድርሻ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። በተጠናቀቀው የ2025 የፈረንጆቹ ዓመት ኤ.አይ በርካታ ስራዎችን መተካቱን አውስተው አሁንም በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ፈጥነን ልጆቻችንን ካዘጋጀን ሰው ሰራሽ አስተውሎትን እንደ ተለያዩ ምርቶች በቀላሉ መጠቀም እንችላለን ብለዋል። ኤ.አይ ስራ ይቀማል ብዬ አልሰጋም ሲሉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሰው ልጅ መስራት የሰው ልጅ ሊሰራቸው የማይገባቸውን ስራዎች እየተካ ይሄዳል ነው ያሉት። ኤ.አይን የምንፈጥር እኛነን ኤ.አይን የምንቀይር እኛ ነን ቀድመን ግን ፋውንዴሽን መጣል ይገባናል ብለዋል። መንግስት ለሰው ሰራሽ አስተውሎት ፖሊሲ እና ስትራቴጂ አዘጋጅቶ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው ሳይንስ ሙዚየም አንዱ መሰረተ ልማት መሆኑን ተናግረዋል። መሰረተ ልማት እና ታለንት ለዘርፉ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱም ነው ያብራሩት። ኢትዮጵያ የምትገነባው የኤ.አይ ዩኒቨርሲቲም የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን ብዙ ችግሮች ይፈታል ተብሎ እንደሚታመን ተናግረዋል። ዋናው ለልጆቻችን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልጆቻችን የሚወዳደሩበት ልጆቻችን ከሌላው አንስው የማይታዩበት ሁኔታ ለመፍጠርም እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ቀድሞ መወዳደር ቀድሞ መገኘት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ኤ.አይን በዛ መልክ ማየት እንደሚገባ ገልጸዋል። ኤ.አይ ስራዎችን በማቃለል እና ጊዜ በመቆጠብ ወሳኝ ድርሻ እንደሚወጡም ነው የገለጹት።   ተማሪዎችም ኤ.አይን መጠቀም አለባቸው፤ ቴክኖሎጂዎቹን መጠየቅ እንዲችሉ አድርገን ከፈጠርናቸው ተማሪዎች ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉ ገልጸዋል። የመጠየቅ ብቃት ችሎታ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ረገድም ኤ.አይ የተማሪዎችን አቅም እንደሚገነባ ተናግረዋል። የመጀመሪያው ትውልድ ለኢኮኖሚ ቅድሚያ የሰጠ እና ሁለተኛው ትውልድ ፖለቲካዊውን ያስቀደመ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሁኑ ዘመን የሀሳብ ትውልድ እንደሆነም ጠቅሰዋል። ሀሳብ የሚወድ ትውልድ ችግሮች እየፈታ እና እያቀለለ እንደሚሄድም ተናግረዋል። ኤ.አይ ዝግጅት እና ስራ እንደሚፈልግ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከመፍራት ይልቅ እውነታውን በመጋፈጥ ማሸነፍ እንችላለን ብለዋል።
ከተማርንና ዝግጁ ከሆንን በኤ አይ የማይናቅ ደረጃ ላይ እንደርሳለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jan 6, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018(ኢዜአ)፡- ከተማርንና ዝግጁ ከሆንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት የማይናቅ ደረጃ ላይ እንደርሳለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በማስመልከት በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ጽሑፍ አቅርበዋል። ጽሑፍ ካቀረቡ በኋላም ከምሁራን ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም፤መንግሥት የኮሪደር ልማትና መንገድ ሠርቶ ለነዋሪው ሲያቀርብ ይህን በአግባቡ እንዴት መያዝ እንደሚቻል ደግሞ ምሁራን ከተሜነትን የሰው ልጅ ዐዕምሮ ላይ መሥራት ይጠበቅባችኋል ብለዋል። ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር በተያያዘም ኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋ ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል። ኤ አይ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ ኢነርጂ መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ ብዙ የማምረት ዐቅም እንዳላት አረጋግጠዋል። ኢነርጂ ላይ ኢንቨስት ካደረግን ለኤ አይ አንድ አስቻይ ጉዳይ ፈታን ማለት ነው ሲሉም ገልጸዋል። ሌላው ኤ አይ የሚፈልገው ጉዳይ መረጃ(ዳታ) እና የመረጃ ማዕከል(ዳታ ሴንተር) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ከተማርን፣ ዝግጁ ከሆንን፣ እየሠራናቸው ያሉትንና በቀጣይ የምናከናውናቸውን ጨምሮ በመተባበር ለለውጥ ዝግጁ ሆነን በትጋት ከሠራን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት የማይናቅ ደረጃ ላይ እንደርሳለን ብለዋል። ለኤ አይ ግብዓት የሚሆኑ ነገሮች በብዛት በአፍሪካ እንደሚገኙም አስገንዝበዋል።
ስፖርት
አማድ ዲያሎ - የአፍሪካ እግር ኳስ  ብሩህ ተስፋ
Jan 9, 2026 69
ተጫዋቹ አዲሱ ሳሙኤል ኤቶ የሚል ስያሜ እየተሰጠው ይገኛል። ፍጥነቱን ከዲዲየር ድሮግባ ጋር ያነጻጽሩታል። ለተጋጣሚ ተጫዋቾች የራስ ምታት እና ፈተና የሆነውን ግራ እግሩን ከሌላኛው የግራ እግር ምትሃተኛ ሪያድ ማህሬዝ ጋር የሚያወዳድሩም አልጠፉም።   በዚህ አካሄዱ ከቀጠለ ያለ ምንም ጥርጥር ወደፊት በእግር ኳስ ከምንመለከታቸው ኮከቦች አንዱ ሊሆን ይችላል እየተባለለት ይገኛል። ይህ ተጫዋች በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ዓመታት ታሪክ ሀትሪክ የሰራ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ተጫዋች ነው። እያወራን የምንገኘው የማንችስተር ዩናይትድ 16 ቁጥር ማልያ ለባሽ አማድ ዲያሎ ነው። የ23 ዓመቱ ኮትዲቯራዊ ተስፈኛ ተጫዋች በቀያዮቹ ሴጣኖች እያሳየ ያለው ብቃት ከብዙዎች ዘንድ ሙገሳ አስችሮታል፣ አድናቆት እንዲጎርፍለት አድርጓል። ወደ ኋላ መለስ እንበልና የአማድ ዲያሎን መነሻ እንመልከት። ካሜሮን ከአዘጋጇ ሞሮኮ ለግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው አማድ የተወለደው እ.አ.አ ጁላይ 11 2002 በኮትዲቭዋር መዲና አቢጃን ነው። ተጫዋቹ በአፍሪካ ምድር ቢወለድም ገና በህጻንነት እድሜው ነበር ወደ ጣልያን የተሰደደው። የእግር ኳስ ህይወቱን የጀመረው እ.አ.አ በ2014 በጣልያን ሬጂዮ ኢሚሊያ ግዛት በሚገኘው ቦካ ባርኮ የታዳጊ ቡድን ነው። ቡድኑን በተቀላቀለበት ዓመት የገና በዓል (ክሪስማስን) በማስመልከት በተካሄደ ውድድር ላይ በ12 ዓመቱ ኮከብ ግብ አግቢ ሲሆን ያሳየው አስደማሚ ብቃት የብዙዎችን ቀልብ ሳበ። ይህ የገና በዓል ውድድር አማድን እ.አ.አ በ2015 በቦካ ባርኮ ቡድን እንዲመዘገብ አደረገው። ተጫዋቹ በቡድኑ ብዙም አልቆየም። የበርካታ የጣልያን ሴሪአ ክለቦች አይን አረፈበት። ብዙም ሳይቆይ በዛው በ2015 ወደ ጣልያኑ አትላንታ አመራ።   አማድ ከእ.አ.አ 2015 እስከ 2019 ለአትላንታ ታዳጊ ቡድን የተጫወተ ሲሆን እ.አ.አ 2019 እና 20 ለዋናው ቡድን ተጫውቷል። ለዋናው ቡድን አራት ጨዋታዎችን አድርጎ ማስቆጠር የቻለው አንድ ግብ ብቻ ነው። የእንግሊዙ ክለብ ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹ በጣልያኑ ክለብ ባሳየው ብቃት በ18 ዓመት እድሜው እ.አ.አ ጃንዋሪ ወር 2021 በአምስት ዓመት ኮንትራት በ37 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዩሮ አስፈርሞታል። ተጫዋቹ ወደ ማንችተር ሲመጣ ቀጥታ ወደ ዋናው ቡድኑ አልተቀላቀለም። በቡድኑ ከ23 ዓመት በታች ጨዋታውን ማድረግ ጀመረ። አማድ የመጀመሪያ ጨዋታውን ለማንችስተር ያደረገው እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 18 2021 ቡድኑ ከሪያል ሶሲዬዳድ ጋር ባደረገው የዩሮፓ ሊግ ጨዋታ ነው። በዛው ዓመት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እና አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ላይ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ዲያሎ ከእ.አ.አ 2022-2023 ባለው ጊዜ ሬንጀርስ እና ሰንደርላንድ በውሰት የተጫወተ ሲሆን በቡድኖቹ ባደረጋቸው 47 ጨዋታዎች 16 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል።   እ.አ.አ በ2023/24 አማድ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ በመመለስ በድጋሚ መጫወት ጀምሯል። በክለቡም ድንቅ ብቃቱን እያሳየ መምጣት ጀመረ። እ.አ.አ ጥር 17 2025 ማንችስተር ዩናይትድ ከሊጉ ከወረደው ሳውዝሃምፐን ጋር በነበረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር በ12 ደቂቃ ውስጥ ሶስት ግቦችን አስቆጥሮ ሀትሪክ በመስራት ቡድኑ 3 ለ 1 አንዲያሸንፍ ያደረገበት መንገድ አድናቆት አስችሮታል። በዚህም አማድ በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ታሪክ የመጀመሪያ ሀትሪክ የሰራ አፍሪካ ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። አማድ በቀያዮቹ ሴጣኖች ማልያ እስከ አሁን ባደረጋቸው 53 ጨዋታዎች 11 ግቦችን አስቆጥሯል። ተጫዋቹ ከክለቡ በተጨማሪ ለኮትዲቯር ብሄራዊ ቡድን በመጫወት ላይ ይገኛል። እ.አ.አ 2021 ኮትዲቯር ከኒጀር ጋር ባደረገችው ጨዋታ በ86ኛው ደቂቃ ተቀይሮ በመግባት ለብሄራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ለሀገሩ እስከ አሁን ባደረጋቸው 15 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። የመጀመሪያ ጎሉን ኮትዲቯር በ2021 በወዳጅነት ጨዋታ ቡርኪናፋሶን 2 ለ 1 ስታሸነፍ ነበር ያስቆጠረው። አማድ ዲያሎ ዘንድሮ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ድንቅ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል። አማድ በውድድሩ ላይ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች ሶስት ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን አንድ ለግብ የሚሆን ግብ አመቻችቶ አቀብሏል። ኮትዲቯር ከሞዛምቢክ፣ ካሜሮን እና ቡርኪናፋሶ ጋር ባደረገቻቸው ጨዋታዎች የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተምርጧል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቯር ሩብ ፍጻሜ እንድትደርስ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። ኮትዲቯር ከግብጽ በሩብ ፍጻሜው ነገ ከግብጽ ጋር ምሽት አራት ሰዓት ላይ በአጋዲር ስታዲየም የምታደርገው ጨዋታ በጉጉጉት ይጠበቃል። ሀገሩ በጠዋታው ላይ ከአማድ ብዙ ትጠብቃለች። ወደ ክለብ እንቅስቃሴው ስንመለስ አማድ በማንችስተር ዩናይትድ ስብስብ ውስጥ ቁልፍ የሚባል ተጫዋች ነው። ፈጣን ኳስን የማንከበላል ክህሎቱ፣ ፍጥነቱ ፣ የቴክኒክ አቅሙ፣ ጨዋታን የማንበብ ብቃቱ እና ሁለቱንም እግሩን የመጠቀም አቅሙ አልፎም ተጫዋቾችን በቄንጥ የሚያልፍበት መንገድ ተጫዋቹን እያስወደሰው ነው። አማድ ዲያሎ ከክንፍ ተጫዋችነቱ ባሻገር የአጥቂ አማካይ ሆኖ መጫወትም ይችላል። እ.አ.አ በ2020 የ18 ዓመት ልደቱን ተከትሎ ተጫዋቹ ስሙን ከአማድ ትራኦሬ ወደ አማድ ዲያሎ አስቀይሯል። አማድ ካለው ድንቅ ብቃት አንጻር ወደፊት በክለብ እና ብሄራዊ ቡድን ደረጃ ድንቅ ጊዜን ካሳለፉ ታዋቂ የአፍሪካ ተጫዋቾች ተርታ የመሰለፉ ጉዳይ አያጠራጥርም።
ሃዋሳ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው 
Jan 9, 2026 62
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 14ኛ ሳምንት ዛሬም ቀጥሎ ሲውል ሶስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ። ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ሃዋሳ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። የሁለት ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ሃዋሳ ከተማ በሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው 13 ጨዋታዎች ስድስት ጊዜ ሲያሸንፍ በአራቱ ተሸንፏል። በቀሪ ሶስት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። በ13ቱ ጨዋታዎች 14 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 10 ጎሎች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ በ21 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ 13 ጨዋታዎችን አከናውኖ በአምስቱ ድል ሲቀናው አራት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል። በአምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 11 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ዘጠኝ ግቦችን አስተናግዷል። ቅዱስ ጊዮርጊስ በ19 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሃዋሳ ከተማ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ቅዱስ ጊዮርስ ከአምስት የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። በሌላኛው መርሃ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ከቀኑ 9 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ድሬዳዋ ከተማ በ17 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ21 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ጨዋታው ሁለቱ ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። መቀሌ 70 እንደርታ ከሸገር ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። መቀሌ 70 እንደርታ በ11 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ሸገር ከተማ በ13 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በጨዋታው መቀሌ 70 እንደርታ ካሸነፈ ከወራጅ ቀጠና ይወጣል። ሸገር ከተማ ከአራት ተከታታይ የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል።
ካሜሮን ከአዘጋጇ ሞሮኮ ለግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
Jan 9, 2026 66
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018 (ኢዜአ)፦ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከሁለት ቀናት እረፍት በኋላ ዛሬ በሩብ ፍጻሜ መርሃ ግብር ይመለሳል። ምሽት አራት ሰዓት ላይ ካሜሮን ከሞሮኮ በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን ትኩረት ስቧል። በጥሎ ማለፉ ካሜሮን ደቡብ አፍሪካን፣ ሞሮኮ ታንዛንያን በማሸነፍ የመጨረሻ ስምንት ውስጥ ገብተዋል። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ ዋንጫ ሲገናኙ የአሁኑ ለአራተኛ ጊዜ ነው። ግብጽ እ.አ.አ በ1986 ባዘጋጀችው 15ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ ሁለት ተገናኝተው አንድ አቻ ተለያይተዋል። ሮጀር ሚላ ለካሜሮን፣ አብዱልከሪም ሜሪ ለሞሮኮ በወቅቱ ግቦቹን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው። እ.አ.አ በ1988 በሞሮኮ በተካሄደው 16ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በግማሽ ፍጻሜው ተጫውተው ካሜሮን በስሪል ቶማስ ማካናኪ ግብ 1 ለ 0 በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። ካሜሮን በፍጻሜው ናይጄሪያን በማሸነፍ ዋንጫውን አንስታለች። ሴኔጋል እ.አ.አ በ1992 ባዘጋጀችው 18ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ ሁለት ተገናኝተው ካሜሮን በአንድሬ ካና-ቢይክ 1 ለ 0 አሸንፋለች። በአጠቃላይ ሁለቱ ቡድኖች በአህጉራዊው መድረክ ሶስት ጊዜ ተገናኝተው ካሜሮን ሁለት ጊዜ ስታሸንፍ አንድ ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። ሁለቱ ሀገራት ከ34 ዓመታት በኋላ ዳግም በአፍሪካ ዋንጫ ተገናኝተዋል። አምስት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን በማንሳት ከግብጽ ቀጥሎ ስኬታማ የሆነችው ካሜሮን እና የአፍሪካ የወቅቱ ምርጥ ቡድን ተብላ የተሰየመችው ሞሮኮ የሚያደርጉት ጨዋታ ጠንካራ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል። አዘጋጇ ሞሮኮ የአፍሪካ ዋንጫን አንድ ጊዜ አንስታለች። የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ ከናይጄሪያ እና አልጄሪያ አሸናፊ ጋር ይጫወታል። በሌላኛው የሩብ ፍጻሜ መርሃ ግብር ማሊ ከሴኔጋል ምሽት አንድ ሰዓት ላይ በታንጀር ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በጥሎ ማለፉ ማሊ ቱኒዚያን፣ ሴኔጋል ሱዳንን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅለዋል። ሀገራቱ በአፍሪካ ዋንጫው ሲገናኙ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ቱኒዚያ እ.አ.አ በ2004 ባዘጋጀችው 24ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ ሁለት ተጫውተው አንድ አቻ ተለያይተዋል። ሃቢብ ፍሬድሪክ ቤይ ለሴኔጋል፣ ድራማኔ ትራኦሬ ለማሊ በወቅቱ ግቦቹን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው። ከ22 ዓመታት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫው ወደ ግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ በሚደረግ ፍልሚያ ይገናኛሉ። ማሊ በአፍሪካ ዋንጫ ትልቅ ውጤቷ በስምንተኛው እና በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችበት ነው። ሴኔጋል አንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። በኮከብ ተጫዋቾች ስብስብ የተሞላችው ሴኔጋል የማሸነፍ ቅድሚያ ግምቱን አግኝታለች። አንድም ጨዋታ ሳታሸንፍ ሩብ ፍጻሜ የደረሰችው ማሊ ለተጋጣሚዋ ጠንካራ ፈተና ትሆናለች ተብሎ ይጠበቃል። የማሊ እና ሴኔጋል አሸናፊ በግማሽ ፍጻሜው ከግብጽ እና ኮትዲቯር አሸናፊ ጋር ይጫወታል።
አካባቢ ጥበቃ
በምስራቅ ሸዋ ዞን ከ400 ሺህ በላይ ሰዎች የሚሳተፉበት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ይካሄዳል
Jan 9, 2026 53
አዳማ፤ ጥር 1 /2018 (ኢዜአ)፡-.በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ከ400 ሺህ በላይ ሰዎች የሚሳተፉበት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት እንደሚካሄድ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ባለፉት አመታት በሕዝብ ተሳትፎ የተከናወኑ የተቀናጁ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራዎች ለተፈጥሮ ሀብት መጠበቅና የከርሰ ምድር ገጸምድር ውሀ ሀብቶች እንዲጎለብቱ አድርጓል። እነዚህን ውጤቶች በማስፋትም በምስራቅ ሸዋ ዞን የተራቆቱ በስነ-አካላዊና ስነ- ህይወታዊ የተፋሰስ ልማት ስራዎች በማከናወን የአፈር ለምነትንና የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም እያገዙ ናቸው። የምስራቅ ሸዋ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንዳሉት በየዓመቱ በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ተጨባጭ ለውጦች ታይተዋል። ይህን ለማሳካትም የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራዎች የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግና የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር የውሀ መጠን መጨመር እንዳስቻሉ ጠቁመዋል። በዞኑ ተግባሩን በማስቀጠልም በዘንድሮ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ 421 ሺህ 651 ሰዎች የሚሳተፉበት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለማካሄድ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል። በዚህም በ270 ተፋሰሶችን ማዕከል በማድረግ 119 ሺህ 495 ሄክታር መሬት እንደሚለማ ተናግረዋል። በዚህም እንቅሰቃሴ ሥነ-አካላዊና ሥነ-ህይወታዊ ስራ በመስራት የተጎዱ መሬቶች እንዲያገግሙ ትኩረት መደረጉን ገልፀዋል፡፡ ይህም በመሬት መራቆት የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ እና የመሬት ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚያስችል ጠቁመዋል። እንዲሁም በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የተጎሳቆለ መሬት ከሰውና እንስሳት በመከለል መልሶ እንዲያገግም ለማድረግ ይሰራል ብለዋል። የዘንድሮውን እቅድ ለማሳካት በየደረጃው በቅንጀት መስራትና በውጤት ማጀብ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማቱም ለ30 ቀናት እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገቷን ከካርቦን ልቀት ነጻ ለማድረግ ዓርአያነት ያለው ተግባር እያከናወነች ነው
Jan 8, 2026 86
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገቷን ከካርቦን ልቀት ነጻ ለማድረግ ለታዳጊ ሀገራት ትልቅ ትምህርት እየሰጠች መሆኗን ዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጀንሲ ገለጸ። አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) በዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ ሆነው የተሰየሙበትን የሹመት ደብዳቤ ለተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ፍራንቸስኮ ላ ካሜራ አቅርበዋል፡፡ በዚሁ ወቅትም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) የተላከን መልዕክት ማቅረባቸው ተገልጿል። ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፉ የኃይል ሽግግር ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነትም ለዋና ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል። ሀገራችን ከምትጠቀመው የኃይል ምንጭ ውስጥ ከ90 በመቶ የሚልቀው ከታዳሽ ኃይል የሚገኝ ነው ያሉት አምባሳደሩ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል መሆኗን አስረድተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የንፋስ፣ የፀሐይ እና የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች ለቀጣናው የኃይል ዋስትና እና ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም እያበረከቱት ያለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦም አስገንዝበዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ ተነሳሽነት እና ወደ ዝቅተኛ የካርቦን ኢኮኖሚ የምታደርገው ሽግግር ለመላው የአፍሪካ አኅጉር ዘላቂ ልማት እንደ ማሳያ የሚያገለግል መሆኑንም አመላክተዋል። ዋና ዳይሬክተር ፍራንቸስኮ ላ ካሜራ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በዘላቂ ልማት ዘርፍ እያሳየች ያለውን ዓርአያነት ያለው አመራር አድንቀው፤ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገቷን ከካርቦን ልቀት ነጻ ለማድረግ ለታዳጊ ሀገራት ትልቅ ትምህርት እየሰጠች ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) እንድታስተናግድ መመረጧ ለዓለም አቀፉ የአየር ንብረት አጀንዳ ያላትን የላቀ ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም በአድናቆት አንስተዋል። ኤጀንሲው ኢትዮጵያ ቅድሚያ በምትሰጣቸው የኃይል ፕሮጀክቶች የቴክኒክ ድጋፍ ለመስጠት እና የኢንቨስትመንት ፋይናንስ ለማሰባሰብ ቁርጠኛ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በዞኑ የተራቆቱ አካባቢዎችን በአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው
Jan 8, 2026 103
ነገሌ ቦረና፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን የተራቆቱ አካባቢዎችን በአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የደን ጥበቃ የስራ ሂደት ቡድን መሪ አቶ አልዬ አረባ እንዳሉት፤ በዞኑ የተራቆቱ አካባቢዎችን በአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው። በአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራውም ከ52 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት የሚሸፍኑ 105 ተፋሰሶች እንደሚለሙ አስረድተዋል፡፡   የተፋሰስ ልማቱን ለማሳካትም 379 የቀበሌ አመራሮችና የልማት ጣቢያ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በዞኑ የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ስራው ከ226 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል፡፡ በበጋ ወራቱ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ እርከንን ጨምሮ ከእንስሳትና ሰው ንኪኪ ነጻ በማድረግ በመጪው ክረምት በአረንጓዴ አሻራ ልማት ለመሸፈን መታቀዱን ተናግረዋል። የተራቆተና የተጎዳ 38 ሺህ 244 ሄክታር የግጦሽ ሳር መሬት ከንክኪ የመከለል ስራም የተፋሰስ ልማቱ አካል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ከበጋው ወራት የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ ጎን ለጎን በክረምቱ የሚተከሉና ጥምር ጥቅም የሚሰጡ 36 ሚሊዮን ችግኞችን የማፍላት ስራ መጀመሩን ተናግረዋል።   ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ልማት ስራዎች በዞኑ ድርቅን በመቋቋም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የራሳቸውን ድርሻ ማበርከታቸውን አመልክተዋል፡፡ የልማት ስራውን ለመጀመር የሚያስችሉ የግብርና መሳሪያዎች በዞኑ ለሁሉም ወረዳዎች መቅረቡን ጠቁመዋል፡፡ ዞኑ ቆላማና ዝናብ አጠር እንዲሁም በድርቅ የሚጠቃ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የእንስሳት እርባታ ስራ በስፋት እንደሚካሄድም ተመላክቷል፡፡
በድሬዳዋ የተከናወኑ የተቀናጁ የተፋሰስ ልማቶች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አግዘዋል 
Jan 8, 2026 73
ድሬዳዋ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተቀናጁ የተፋሰስ ልማቶች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ማገዛቸውን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። በአስተዳደሩ ባለፉት የለውጥ ዓመታት 56ሺህ ሄክታር የተራቆቱ መሬቶችን በተፋሰሶች በማልማት የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭን ስኬታማ ማድረጉም ተመልክቷል። የፊታችን ጥር 3 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬዳዋ 38 የገጠር ቀበሌዎች የሚጀመረውን የተፋሰስ ልማት አስመልክቶ ለአስተዳደሩ አመራሮችና ነዋሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል።   በመድረኩ የተገኙት ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በድሬዳዋ የተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የጎርፍ አደጋዎችን ከማስቀረት ባለፈ የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭን ስኬታማ አድርገዋል። በተለይም በገጠሩ አካባቢ የተከናወኑ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ተፋሰሶች የአፈር ለምነትን ለመመለስና የገጸ ምድርና ከርሰ ምድር የውሃ ሀብት እንዲጨምር ማድረጋቸውን አንስተዋል። በተጨማሪም የጎርፍ ውሃን ለአነስተኛ መስኖ ልማቶች በማዋል ህብረተሰቡ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ እያስቻሉ ይገኛሉ ብለዋል። ይህን ተሞክሮ በማስቀጠል በዘንድሮው የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት በየደረጃው የሚገኘው አመራርና ህብረተሰቡ በመረባረብ እንዲያሳካም አስገንዝበዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኑረዲን አብደላ በሰጡት መግለጫ፤ በሚቀጥለው እሁድ በ 5 ሺህ 550 ሄክታር የተራቆቱ ተፋሰሶች ላይ የተለያዩ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራዎች እንደሚጀመር ተናግረዋል።   በ38ቱ የአስተዳደሩ የገጠር ቀበሌዎች ለአንድ ወር የሚከናወነው የተፋሰስ ልማት ከአፈርና ውሃ ጥበቃ ተግባራት በተጨማሪ ለመጪው ክረምት ለሚተከሉ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኞች ጉድጓዶች ይዘጋጃሉ ብለዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት 56 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተካሄዱት የተፋሰስ ልማቶች የገጠሩን ህብረተሰብ የግብርናና የእንስሳት ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እያሸጋገሩ መሆኑን አንስተዋል። የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ስኬታማ በመሆኑ የማር፣ የወተት፣ የዶሮና የእንቁላል ምርቶችን ማሳደግ ማስቻሉን ጠቅሰው ይህም ህብረተሰቡ ተመጣጣኝ ምግብ እና ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ ማስቻሉን አስረድተዋል።   ዘንድሮ ከተፋሰሱ ልማት ጎን ለጎን የገጠሩን ህብረተሰብ በሙሉ የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት የማድረግ ስራ በትኩረት እንደሚሰራ የገለፁት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ኢብራሂም ዩሱፍ ናቸው። አቶ ኢብራሂም አክለው እንዳሉት የገጠሩን ህብረተሰብ የኮሪደር ልማት ባለቤት የማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራም ይከናወናል። ጥር 3 ቀን 2018ዓ.ም በሚጀመረው የተፋሰስ ልማት ስራ ላይ ከ37 ሺህ በላይ አርሶ እና አርብቶ አደሮች እንደሚሳተፉ ተመላክቷል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የቻይና አፍሪካ ትብብር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል
Jan 8, 2026 61
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማሕሙድ አሊ ዩሱፍ ከቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ጋር ውይይት አካሄዱ። ውይይቱ እያደገ የመጣው የቻይና አፍሪካ ትብብርን ማጠናከር ላይ ያለመ ነው ተብሏል። ቻይና የአፍሪካ እውነተኛ አጋር መሆኗን የገለፁት የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ያተኮረው ፖሊሲ ጠንካራ ወዳጅነት እንዲፈጠር ማድረጉን ገልፀዋል። የቻይና አፍሪካ ግንኙነት በተለያዩ የትብብር ማዕቀፎች እያደገ መምጣቱንም ተናግረዋል። ከውይይቱ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ሁለቱ ወገኖች የዓለም ደቡባዊ ቀጣና (Global South) ሀገራትን መብትና ጥቅም ለማስከበር፣ የሉዓላዊነትን ክብር ለመጠበቅ እና ዓለም አቀፍ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በጋራ ለመሥራት መስማታቸውን አስታውቀዋል። በውይይቱ ወቅት የቻይናን የአምስት ዓመት የልማት ዕቅድ ከአፍሪካ ኅብረት የ2063 አጀንዳ ሁለተኛው የዐሥር ዓመት ትግበራ ጋር በማጣጣም ዘመናዊነትን ለማምጣት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ምክክር መደረጉ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነቶችን ጨምሮ፣ ቻይና ያቀረበቻቸውን ዓለም አቀፍ የደኅንነትና የልማት ተነሳሽነቶች በጋራ ለመደገፍ ከስምምነት መድረሳቸውን ኢቢሲ ዘግቧል። በተጨማሪም የተፈረሙ የትብብር ስምምነቶችን በተግባር በመተርጎም እና የንግድ ልውውጥን በማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት በጋራ መግለጫቸው አረጋግጠዋል።
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ በቀጣዩ ሳምንት ይጀመራል
Jan 8, 2026 85
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ(PRC) መደበኛ ስብሰባው ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ያተኮረ ነው። በስብሰባው የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብሰባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብሰባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት፤ የአፍሪካ ህብረት የ2026 መሪ ሀሳብ ዋና የትኩረት አጀንዳ
Dec 26, 2025 595
39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ነው። መሪ ሀሳቡን ያረቀቀው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የዘንድሮው መሪ ቃል ከአጀንዳ 2063 ጋር የተቆራኘ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። ሁሉም አፍሪካዊ ንጹህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በቂ ውሃ ለመጠጥ፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና ለሌሎች ፍላጎቶቹ እንዲያገኝ የማድረግ ራዕይን ለማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል።   ህብረቱ የውሃ ደህንነት እንደ አህጉር የተያዙ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን በማዕቀፎቹ አስቀምጧል። ውሃ እና ንጽህና የኢኮኖሚ እድሎችን በማስፋት፣ የስራ አጥነት ምጣኔን በመቀነስ፣ የስደቶችና ተፈናቃዮችን ጫና ለማቃለል እንዲሁም ለሰላምና ደህንነት መስፈን አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተመላክቷል። የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ህብረቱ ውሃ እና ንጽህና ለጤና፣ ለኢኮኖሚ እድገት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥና ዘላቂ የአካባቢ ምህዳር ለመፍጠር መሰረት መሆኑን የበለጠ እውቅና እንደተሰጠው አመልክቷል። ሁሉን አቀፍ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይገበር የውሃ ደህንነትን የማረጋገጥ አላማ ካለው የአፍሪካ የውሃ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው። የዘንድሮው መሪ ቃል የአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ጥረቶችን ያስተሳሰረ ድልድይ ሆኗል። በዘላቂ ልማት ግቦች ውስጥ ያለው ግብ ስድስት ከውሃ እና ንጽህና ጋር የተያያዘ ነው። ይህ ግብ እ.አ.አ በ2030 ለሁሌም ዜጋ ደህንነቱ የተረጋገጠ ውሃ አቅርቦትና የንጽህና አጠባበቅን ተደራሽ የማድረግ አላማ አለው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት በፍጥነት መስፋፋትና ውሃ በአግባቡ አለመጠቀም የውሃ ደህንነት እና ዘላቂ አቅርቦት ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። የንጽህና አጠባበቅ የአፍሪካ አንዱ ፈተና ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች መሰረታዊ የሚባል የንጽህና መጠበቂያ መሰረተ ልማቶችን አያገኙም። ይህም እንደ ኮሌራ ላሉ የውሃ ወለድ በሽታዎች መስፋፋት ምክንያት ሆኗል። የተቀናጀ የውሃ አስተዳደር ስርዓት፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ ለዘላቂ መሰረተ ልማት የሚፈሰወን መዋዕለ ንዋይን ማሳደግ፣ ውሃ በድጋሚ አጣርቶ መጠቀም፣ የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ፣ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር እና ለውሃ ደህንነት ትኩረት የሚሰጡ ፖሊሲዎችና ማዕቀፎችን በውጤታማነት መተግበር ያሉትን እድሎች በዘላቂነት ለመፍታትና ፈተናዎችን ለመቅረፍ ያስችላል። ደህንነቱ የተረጋገጠ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ላይ ያለፈውን ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የቆሸሸ ውሃ በአግባቡ ማከም፣ የንጽህና አጠባበቅ ማስፋትና የግንዛቤ ፈጠራ ስራን በስፋት ማከናወን፣ ማህበረሰብ መር የንጽህና አጠባበቅ ኢኒሼቲቮችን ትግበራ ማስፋት፣ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎችና ሀገር በቀል አቅምን መገንባት ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓትን መፍጠር ያስችላል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና ጤናማ ማህበረሰብ ግንባታ ያላቸውን ቁልፍ ሚና የሚያሳይ ነው። የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ማድረግ መሰረታዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ ለማህበረሰብ ደህንነትና የተሻለ የኑሮ ዘይቤ፣ ለአካባቢ ጥበቃና ለአፍሪካ ብልጽግና መረጋገጥ ስትራቴካዊ አቅም ናቸው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በሚካሄድበት ወቅት በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም እና 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኞች ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳሉ። ኢትዮጵያ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የአፍሪካ ጣሊያን ስብሰባን ለማዘጋጀት ብሄራዊ የዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቀን ነው - የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Dec 24, 2025 502
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ሲል የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ገለጸ። የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በኤርትራ መንግሥት አገዛዝ ደረሰብን ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ጋምቢያ(ባንጁል) የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ላቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን አድንቋል። በኤርትራ መንግስት ላይ የቀረቡትን ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክስ ተቀብሎ በመዝገብ ቁጥር 868/25 መመዝገቡን፣ የክሱ ፍሬ ነገር እና ይዘት ተቀባይነት ያለው መሆኑን እውቅና በመስጠት የኤርትራ መንግስት እንዲመልስ ክሱን መላኩን ኮሚሽኑ ማስታወቁን ገልጿል። የድርጅቱ ሊቀ-መንበር ኢብራሂም ሀሩን በመግለጫቸው እንደተናገሩት፤ የኤርትራው መንግሥት በደናክል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ህዝቦች እየፈፀመ ያለው መጠነ ሰፊ፣ ስልታዊ፣ መንግስታዊ መር እና ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በአሁኑ ወቅት እየደረሱ ነው ካሏቸው የመብት ጥሰቶች መካከልም ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ማካሄድ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት፣ በሺዎች የሚቆጠሩትን መሰወር፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ማከናወን መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰው፤ በተለይም ከ300ሺህ በላይ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማፈናቀል እና ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል፣ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋትና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን መጣስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ድርጅቱ የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ከ1993 ጀምሮ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰባቸው ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ክስ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እኤአ ጁን 04 ቀን 2025 በ122 ገጽ የተደራጀ ክስ ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የኤርትራ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን እንደገለጸላቸው ጠቁመዋል። ለክሱም ከተጠቀሙት ማስረጃዎች መካከል በድርጅቱ የተከናወነ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ግኝት፣ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝባዊ መብቶች በኤርትራ ላይ የተደረጉ ምርመራዎች፣ ግኝቶችና ማስረጃዎች፣ የመብት ጥሰት የደረሰባቸው የቀይ ባሕር አፋር ተጎጂ ወገኖች እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የተገኙ የሰብዓዊ መብት ምርመራዎችን መቅረቡን ተናግረዋል። ድርጅቱ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት መከራ ለማዳን፣ የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ድምፅ እንዲሆኑት፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡንና የኢሳያስ መንግስት ላይ ህጋዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 422
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 404
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።  
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 624
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 780
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል።   ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ።   ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡   የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።  
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 380
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል።   ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር።   ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ።   ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ   ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ   ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።   ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው።   መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ 
Jan 1, 2026 353
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው።   በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል።   ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ   ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 1023
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3367
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 2955
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1876
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7696
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6175
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 59492
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53611
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34257
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31794
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27236
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26092
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25637
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25529
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 59492
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 53611
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 34257
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 31794
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
አማድ ዲያሎ - የአፍሪካ እግር ኳስ  ብሩህ ተስፋ
Jan 9, 2026 70
ተጫዋቹ አዲሱ ሳሙኤል ኤቶ የሚል ስያሜ እየተሰጠው ይገኛል። ፍጥነቱን ከዲዲየር ድሮግባ ጋር ያነጻጽሩታል። ለተጋጣሚ ተጫዋቾች የራስ ምታት እና ፈተና የሆነውን ግራ እግሩን ከሌላኛው የግራ እግር ምትሃተኛ ሪያድ ማህሬዝ ጋር የሚያወዳድሩም አልጠፉም።   በዚህ አካሄዱ ከቀጠለ ያለ ምንም ጥርጥር ወደፊት በእግር ኳስ ከምንመለከታቸው ኮከቦች አንዱ ሊሆን ይችላል እየተባለለት ይገኛል። ይህ ተጫዋች በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ዓመታት ታሪክ ሀትሪክ የሰራ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ተጫዋች ነው። እያወራን የምንገኘው የማንችስተር ዩናይትድ 16 ቁጥር ማልያ ለባሽ አማድ ዲያሎ ነው። የ23 ዓመቱ ኮትዲቯራዊ ተስፈኛ ተጫዋች በቀያዮቹ ሴጣኖች እያሳየ ያለው ብቃት ከብዙዎች ዘንድ ሙገሳ አስችሮታል፣ አድናቆት እንዲጎርፍለት አድርጓል። ወደ ኋላ መለስ እንበልና የአማድ ዲያሎን መነሻ እንመልከት። ካሜሮን ከአዘጋጇ ሞሮኮ ለግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው አማድ የተወለደው እ.አ.አ ጁላይ 11 2002 በኮትዲቭዋር መዲና አቢጃን ነው። ተጫዋቹ በአፍሪካ ምድር ቢወለድም ገና በህጻንነት እድሜው ነበር ወደ ጣልያን የተሰደደው። የእግር ኳስ ህይወቱን የጀመረው እ.አ.አ በ2014 በጣልያን ሬጂዮ ኢሚሊያ ግዛት በሚገኘው ቦካ ባርኮ የታዳጊ ቡድን ነው። ቡድኑን በተቀላቀለበት ዓመት የገና በዓል (ክሪስማስን) በማስመልከት በተካሄደ ውድድር ላይ በ12 ዓመቱ ኮከብ ግብ አግቢ ሲሆን ያሳየው አስደማሚ ብቃት የብዙዎችን ቀልብ ሳበ። ይህ የገና በዓል ውድድር አማድን እ.አ.አ በ2015 በቦካ ባርኮ ቡድን እንዲመዘገብ አደረገው። ተጫዋቹ በቡድኑ ብዙም አልቆየም። የበርካታ የጣልያን ሴሪአ ክለቦች አይን አረፈበት። ብዙም ሳይቆይ በዛው በ2015 ወደ ጣልያኑ አትላንታ አመራ።   አማድ ከእ.አ.አ 2015 እስከ 2019 ለአትላንታ ታዳጊ ቡድን የተጫወተ ሲሆን እ.አ.አ 2019 እና 20 ለዋናው ቡድን ተጫውቷል። ለዋናው ቡድን አራት ጨዋታዎችን አድርጎ ማስቆጠር የቻለው አንድ ግብ ብቻ ነው። የእንግሊዙ ክለብ ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹ በጣልያኑ ክለብ ባሳየው ብቃት በ18 ዓመት እድሜው እ.አ.አ ጃንዋሪ ወር 2021 በአምስት ዓመት ኮንትራት በ37 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዩሮ አስፈርሞታል። ተጫዋቹ ወደ ማንችተር ሲመጣ ቀጥታ ወደ ዋናው ቡድኑ አልተቀላቀለም። በቡድኑ ከ23 ዓመት በታች ጨዋታውን ማድረግ ጀመረ። አማድ የመጀመሪያ ጨዋታውን ለማንችስተር ያደረገው እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 18 2021 ቡድኑ ከሪያል ሶሲዬዳድ ጋር ባደረገው የዩሮፓ ሊግ ጨዋታ ነው። በዛው ዓመት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እና አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ላይ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ዲያሎ ከእ.አ.አ 2022-2023 ባለው ጊዜ ሬንጀርስ እና ሰንደርላንድ በውሰት የተጫወተ ሲሆን በቡድኖቹ ባደረጋቸው 47 ጨዋታዎች 16 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል።   እ.አ.አ በ2023/24 አማድ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ በመመለስ በድጋሚ መጫወት ጀምሯል። በክለቡም ድንቅ ብቃቱን እያሳየ መምጣት ጀመረ። እ.አ.አ ጥር 17 2025 ማንችስተር ዩናይትድ ከሊጉ ከወረደው ሳውዝሃምፐን ጋር በነበረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር በ12 ደቂቃ ውስጥ ሶስት ግቦችን አስቆጥሮ ሀትሪክ በመስራት ቡድኑ 3 ለ 1 አንዲያሸንፍ ያደረገበት መንገድ አድናቆት አስችሮታል። በዚህም አማድ በማንችስተር ዩናይትድ የ147 ታሪክ የመጀመሪያ ሀትሪክ የሰራ አፍሪካ ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። አማድ በቀያዮቹ ሴጣኖች ማልያ እስከ አሁን ባደረጋቸው 53 ጨዋታዎች 11 ግቦችን አስቆጥሯል። ተጫዋቹ ከክለቡ በተጨማሪ ለኮትዲቯር ብሄራዊ ቡድን በመጫወት ላይ ይገኛል። እ.አ.አ 2021 ኮትዲቯር ከኒጀር ጋር ባደረገችው ጨዋታ በ86ኛው ደቂቃ ተቀይሮ በመግባት ለብሄራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። ለሀገሩ እስከ አሁን ባደረጋቸው 15 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። የመጀመሪያ ጎሉን ኮትዲቯር በ2021 በወዳጅነት ጨዋታ ቡርኪናፋሶን 2 ለ 1 ስታሸነፍ ነበር ያስቆጠረው። አማድ ዲያሎ ዘንድሮ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ድንቅ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል። አማድ በውድድሩ ላይ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች ሶስት ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን አንድ ለግብ የሚሆን ግብ አመቻችቶ አቀብሏል። ኮትዲቯር ከሞዛምቢክ፣ ካሜሮን እና ቡርኪናፋሶ ጋር ባደረገቻቸው ጨዋታዎች የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተምርጧል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቯር ሩብ ፍጻሜ እንድትደርስ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። ኮትዲቯር ከግብጽ በሩብ ፍጻሜው ነገ ከግብጽ ጋር ምሽት አራት ሰዓት ላይ በአጋዲር ስታዲየም የምታደርገው ጨዋታ በጉጉጉት ይጠበቃል። ሀገሩ በጠዋታው ላይ ከአማድ ብዙ ትጠብቃለች። ወደ ክለብ እንቅስቃሴው ስንመለስ አማድ በማንችስተር ዩናይትድ ስብስብ ውስጥ ቁልፍ የሚባል ተጫዋች ነው። ፈጣን ኳስን የማንከበላል ክህሎቱ፣ ፍጥነቱ ፣ የቴክኒክ አቅሙ፣ ጨዋታን የማንበብ ብቃቱ እና ሁለቱንም እግሩን የመጠቀም አቅሙ አልፎም ተጫዋቾችን በቄንጥ የሚያልፍበት መንገድ ተጫዋቹን እያስወደሰው ነው። አማድ ዲያሎ ከክንፍ ተጫዋችነቱ ባሻገር የአጥቂ አማካይ ሆኖ መጫወትም ይችላል። እ.አ.አ በ2020 የ18 ዓመት ልደቱን ተከትሎ ተጫዋቹ ስሙን ከአማድ ትራኦሬ ወደ አማድ ዲያሎ አስቀይሯል። አማድ ካለው ድንቅ ብቃት አንጻር ወደፊት በክለብ እና ብሄራዊ ቡድን ደረጃ ድንቅ ጊዜን ካሳለፉ ታዋቂ የአፍሪካ ተጫዋቾች ተርታ የመሰለፉ ጉዳይ አያጠራጥርም።
በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ብዙ ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን ያቀበሉ ተጫዋቾች
Jan 5, 2026 178
በእግር ኳስ ጨዋታ ከግብ አስቆጣሪዎች ጀርባ ኳስን ፍትፍት አርገው ጨርሰው የሚያቀብሉ ተጫዋቾች አሉ። አንድ ተጫዋች ግብ ሲያገባ ከማግባቱ ባልተናነሰ ማን ኳሱን አቀበለው? የሚለው ጥያቄ በተመልካቾች ይነሳል። በእግር ኳስ እድገት ውስጥ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለጎል ኳስ አመቻችተው የሚያቀብሉ ተጫዋቾች ትልቅ ዋጋ ይሰጣቸዋል። ማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪምን አሰናበተ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች እየተካሄዱ ይገኛሉ።   የ33 ዓመቱ የሴኔጋል አምበል ሳዲዮ ማኔ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ካስቆጠረው አንድ ግብ በተጨማሪ ሶስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል የቀዳሚነቱን ስፍራ ይዟል። ማኔ ሴኔጋል ለሩብ ፍጻሜ እንድታልፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ ትልቅ የሚባል ነው። ስምንት ተጫዋቾች በተመሳሳይ ሁለት ለግብ የሚሆኑ ግቦችን አመቻችተው አቀብለዋል።   ናይጄሪያውያኑ አዴሞላ ሉክማን እና አሌክስ ኢዎቢ፣ የሞሮኮው አዝዲን ኡናሂ፣ የአልጄሪያው አኒስ ሃጂ-ሙሳ፣ የቡርኪናፋሶው ዳንጎ ኡታራ፣ የቱኒዚያው ሃኒባል ሜጅብሪ፣ የደቡብ አፍሪካው ላይል ፎስተር እና የታንዛንያ ኖቫቱስ ሞሮሺ በሁለት ግቦች ላይ እጃቸው ያለበት ተጫዋቾች ናቸው።   የናይጄሪያው የክንፍ የመስመር ተጫዋች አዴሞላ ሉክማን ሁለት ግቦችን በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አስቆጥሯል።   የኮትዲቯሩ ክርስቶፈር ኦፔሪ እና የናይጄሪያው ሳሙኤል ቹኩዌዜ በተመሳሳይ አንድ አንድ ግቦች ከመረብ ላይ እንዲቆጠሩ የቀጥታ ተሳትፎ አድርገዋል።   የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬን (ካፍ) የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ኮከብ ተጫዋች ምርጫ ላይ ካስቀመጣቸው መመዘኛ መስፈርቶች አንዱ ማን ብዙ ለጎል የሚሆን አቀበለ? የሚለው ይገኝበታል። 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እስከ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የግብ አግቢዎችና የኳስ አቀባዮቹ ፉክክር በያዘው ግለት ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም