ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በተጠባቂው ጨዋታ ባርሴሎና አትሌቲኮ ማድሪድን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ
Dec 3, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ በስፔን ላሊጋ ሳምንት የ15ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ባርሴሎና አትሌቲኮ ማድሪድን 3 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በካምፕ ኑ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ራፊኒያ፣ ዳኒ ኦልሞ እና ፌራን ቶሬስ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። አሌክስ ባኤና ለአትሌቲኮ ማድሪድ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው ላይ ባርሴሎና ያገኘውን ፍጹም ቅጣት ምት ሮበርት ሌዋንዶስኪ ሳይጠቀምበት ቀርቷል። በሊጉ 12ኛ ድሉን ያስመዘገበው ባርሴሎና በ37 ነጥብ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል። ከተከታዩ ሪያል ማድሪድ ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አትሌቲኮ ማድሪድ በ31 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። በ33 ነጥብ በሊጉ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሪያል ማድሪድ ነገ ከሜዳው ውጪ ከአትሌቲኮ ቢልባኦ ጋር ያደርጋል።
ዘጠኝ ግቦች በተቆጠሩበት አዝናኝ ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን አሸነፈ
Dec 3, 2025 47
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 5 ለ 4 አሸንፏል። ማምሻውን በክራቫን ኮቴጅ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፊል ፎደን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር አርሊንግ ሃላንድ፣ ታጃኒ ራይንደርስ እና የፉልሃሙ ሳንደር በርገ በራሱ ላይ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ሳሙኤል ቹኩዌዜ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ኤሚል ስሚዝ ሮው እና አሌክስ ኢዎቢ ቀሪዎቹን ግቦች ለፉልሃም አስቆጥረዋል። ማንችስተር ሲቲ 5 ለ 1 እየመራ ሶስት ግቦችን ማስተናገዱ በጨዋታው ማብቂያ ላይ ውጥረት ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል። በሊጉ ዘጠነኛ ድሉን ያስመዘገበው ማንችስተር ሲቲ በ28 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ፉልሃም በ17 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ 100ኛ ግቡን አስቆጥሯል። ሃላንድ በሊጉ ፈጣን 100 ግብ አስቆጣሪ በመሆን አዲስ ታሪክ ሰርቷል። ተጫዋቹ ግቦቹን ከመረብ ላይ በማሳረፍ 111 ጨዋታዎች ወስዶበታል። ከዚህ ቀደም አለን ሺረር በ124 ጨዋታዎች 100 ግቦችን በማስቆጠር ለ30 ዓመታት ክብረ ወሰኑን ይዞ ቆይቷል። በሌሎች መርሃ ግብሮች ኤቨርተን በጃክ ግሪሊሽ ጎል ቦርንማውዝን ከሜዳው ውጪ 1 ለ 0 አሸንፏል። ኒውካስትል ዩናይትድ እና ቶተንሃም ሆትስፐርስ ያደረጉት ጨዋታ ሁለት አቻ ተጠናቋል። ብሩኖ ጉማራይሽ በጨዋታ እና አንቶኒ ጎርደን በፍጹም ቅጣት ምት ለኒውካስትል ግቦቹን አስቆጥረዋል ። ክርስቲያን ሮሜሮ ለቶተንሃም ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፏል።
ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድኑ የ10 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበረከተ
Dec 2, 2025 126
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ):- የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ለአፍሪካ ዋንጫ ላለፈው ለኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን የ10 ሚሊዮን ብር የገንዝብ ሽልማት አበርክቷል። ሚኒስቴሩ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድኑ ማምሻውን የእራት ግብዣ አድርጓል። ሚኒስቴሩ በመርሐ ግብሩ ላይ የ10 ሚሊዮን ብር ሽልማት ለብሄራዊ ቡድኑ ያበረከተ ሲሆን የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ የገንዘብ ሽልማቱን አስረክበዋል። ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በወቅቱ የተገኘው ስኬት የመንግስትና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የጋራ ስራ ውጤት እንደሆነ ተናግረዋል። ብሄራዊ ቡድኑ በአፍሪካ ዋንጫው ተሳትፎው ውጤታማ ጊዜ እንዲያሳልፍ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል። በመርሐ ግብሩ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጅራ እና ሌሎች የፌዴሬሽኑ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ማጣሪያ ዛሬ ከኬንያ አቻው ጋር ባደረገው የደረጃ ጨዋታ 3 ለ 0 በማሸነፍ ለአህጉራዊው መድረክ ማለፉን አረጋግጧል። ብሄራዊ ቡድኑ ከ22 ዓመታት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ይመለሳል። ኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ውድድር ላይ ስትሳተፍ የሞሮኮው ለአራተኛ ጊዜ ነው።
በፕሪሚየር ሊጉ ነጌሌ አርሲ እና ሸገር ከተማ አቻ ተለያዩ
Dec 2, 2025 69
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የስምንተኛ ሳምንት መርሐግብር ነጌሌ አርሲ እና ሸገር ከተማ ያደረጉት ጨዋታ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ማምሻውን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጀቤሳ ሚኤሳ በ55ኛው እና በ70ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ሸገር ከተማ መሪ ሆኖ ነበር። ይሁንና ከቤ ብዙነህ በ75ኛው እና ሮሆቦት ሰላሎ በ93ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፏቸው ጎሎች ነጌሌ አርሲን አቻ አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ ነጌሌ አርሲ በ10 ነጥብ ደረጃውን ከ12ኛ ወደ 11ኛ ከፍ አድርጓል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ሸገር ከተማ በዘጠኝ ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታውን ተከትሎ የስምንተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የዘጠነኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከሕዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳሉ።
ብሔራዊ ባንክ ያካሄደው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ይፋ ሆነ
Dec 2, 2025 107
አዲስ አበባ፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ያካሄደውን የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ይፋ አድርጓል። በጨረታ ሂደቱ 17 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን በዚህም የምንዛሪ ጨረታ አንድ የአሜሪካን ዶላር ዋጋ በአማካኝ 154 ነጥብ 3993 ብር ሆኖ መመዝገቡ ተገልጿል፡፡ ቀጣዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።
ፖለቲካ
በምስራቅ ጎጃም ዞን ሰላምን በማጽናትና ልማትን በማረጋገጥ በህዝቡ የታየው ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Dec 2, 2025 147
ደብረ ማርቆስ፤ ህዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ሰላምን በማጽናትና ልማትን በማረጋገጥ ረገድ በህዝቡ ዘንድ የታየው እገዛና ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ በሰላምና በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በደብረ ማርቆስ ከተማ ከነዋሪዎችና ከተለያዩ የህብረተሰቡ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በክልሉ የጥፋት ተልእኮ በመያዝ ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር፣ የልማት ስራዎች እንዳይሳኩና ማህበራዊ አገልግሎቶች እንዲስተጓጎሉ ፅንፈኞች ጥረት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የጽንፈኛ ቡድኑ የጥፋት ተልእኮ ግን በህዝቡ ጠንካራ ትብብርና በጸጥታ ኃይሉ ህግ የማስከበር እንቅስቃሴ በሁሉም አካባቢዎች ሰላምና መረጋጋት ማስፈን ተችሏል ብለዋል። ለዚህም የህዝቡ ትብብር፣ እገዛና ጽኑ የሰላም ፍላጎት ታክሎበት ችግሩን መፍታት ስለመቻሉ አንስተው ሰላምን በማጽናትና ልማትን በማረጋገጥ ረገድ የህዝቡ እገዛና ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢዎች ያለውን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል መንግስት እየሰራ መሆኑን ገልጸው የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም ሰላማዊ ህይወት እንዲመሩ እየተደረገ ነው ብለዋል። አሁንም ቢሆን በጫካ የሚገኙ የታጠቁ ቡድኖች የሰላም እድሉን ከተጠቀሙ ምንጊዜም በሩ ክፍት ስለመሆኑ አረጋግጠዋል። ከዚህ ባለፈ ግን ሰላምን የማስጠበቅና ልማትን የማረጋገጥ ስራ በተቀናጀና በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ፤ ከነዋሪዎች ጋር በመተባበር በተሰራው ስራ የከተማዋ ሰላም በመልካም ሁኔታ ላይ እንዲገኝ አስችሏል ብለዋል። የዚህ መድረክ ዓላማም የተገኘውን ሰላም ማጽናትና የተጀመሩ የልማት ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል መሆኑን ገልጸዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ እስራኤል እምባቆም እና ወይዘሮ መስከረም ታደገ፤ የሰላም ጉዳይ በጋራ አቋም ይዘን የምንሰራበት በመሆኑ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ተሳትፈዋል።
የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል- የቀድሞ ታጣቂዎች
Dec 2, 2025 141
ገንዳ ውሃ ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ የተሳሳተ መንገድ ተከትለው በፈፀሙት ጥፋት በመፀፀት የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ መዘጋጀታቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን የሰላም አማራጭ ተቀብለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ በዳንስ ጉንዶ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተቀብለው በመመለስ ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት አስረክበዋል። ከእነዚህም መካከል መብራቱ አወቀ በሰጠው አስተያየት፤ በተሳሳተ መንገድ ለጥፋት በመንቀሳቀስ ሕዝቡንና አካባቢውን ለችግር በማጋላጣቸው መፀፀቱን ተናግሯል። ችግርን በሰላማዊ ውይይት መፍታት ሲገባ ግጭት በመቀስቀስ ጥፋት መፈፀም ተገቢነት እንደሌለው በመገንዘብ የሰላም አማራጭ መቀበላቸውን አመልክቶ፤ የተሳሳተ መንገድ ተከትለን በፈፀምነው ጥፋት ተፀፅተን የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል ብሏል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል አብረውት ከነበሩት ጋር መመለሳቸውን የገለጸው ደግሞ ሌላው የቀድሞ ታጣቂ አየነው ውበት ነው። የተሳሳተ መንገድ በመከተል ሕዝባችንን ለችግር ዳርገናል ፤ በዚህ በመፀፀት የበደልነውን ሕዝብ በልማት ለመካስ ተዘጋጅተናል ሲል ገልጿል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ እንደገለጹት፤ የዞኑን ብሎም የክልሉን ሰላም ለማፅናት በቁርጠኝነት እየተሰራ ነው። መንግስት የሰጣቸውን የሰላም እድል እንዲጠቀሙ በተደረገው ጥረት የሰላም አማራጭን በመቀበል ቀደም ሲል የተመለሱ የተሃድሶ ስልጠና ተሰጥቷቸው ህይወታቸውን እየለወጡ መሆኑን አስረድተዋል። አሁንም የሰላም አምባሳደር ሆነው የመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችን የዞኑ መስተዳድርና ሕዝብ አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት በፈለጉት የሙያ መስክ እንዲሰማሩ ይደረጋል ብለዋል። በመከላከያ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ የ504ኛ ኮር ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ቾቤ ወርቁ በበኩላቸው፤ መንግስት ለሰላም ሁሌም በሩ ክፍት ነው ብለዋል። ሕብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት መረጃ በመስጠትና ችግር ወስጥ የገቡትን ወደ ሰላም እንዲመጡ በማድረግ እያበረከተ ላለው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበው ፤ በቀጣይም ይህ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።
ኮሚሽኑ የምክክር ጉባዔው የሚመክርባቸውን አጀንዳዎች ቀርጾ ይፋ ማድረግና ጉባዔውን ለመጥራት ዝግጅቱን እያጠናቀቀ ነው
Dec 2, 2025 194
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የምክክር ጉባዔው የሚመክርባቸውን አጀንዳዎች ቀርጾ ይፋ ማድረግና ጉባዔውን ለመጥራት ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። ወደዚሁ ወሳኝ ምዕራፍ ለመሸጋገር መከናወን ያለባቸው ወሳኝ ቀሪ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ''የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማትና የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ተሳትፎ ለሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት'' በሚል መሪ ሃሳብ የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኮሚሽኑ ምክክሩ ሁሉን አሳታፊና አካታች ለማድረግ ለተሳታፊ ልየታ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል፡፡ የኅብረተሰብ ክፍሎችን፣የሃይማኖት እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ጨምሮ በርካታ ተቋማትና ማህበራትን፣ ታዋቂ ሰዎችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲሁም መንግሥትን በተወካዮቻቸው አማካኝነት ማካተትና ማሳተፍ መቻሉም ገልጸዋል። በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይወሰንም የዳያስፖራ ወገኖችም በሂደቱ እንዲሳተፉ ጥረት መደረጉን አንስተዋል። ኮሚሽኑ አሁን ላይ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው የሚመክርባቸውን አጀንዳዎች ቀርጾ ይፋ ማድረግና ጉባዔውን ለመጥራት ጫፍ ላይ መድረሱን አስታውቀው፤ ለዚህም ቅድመ ዝግጅቶችን እያደረገ እንደሚገኝ አመላክተዋል። ወደዚሁ ወሳኝ ምዕራፍ ለመሸጋገር መከናወን ያለባቸው ወሳኝ ቀሪ ተግባራት አሉ ያሉት ዋና ኮሚሽነሩ፤ የትግራይ ክልል ሕዝብና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አጀንዳቸውን የሚሰጡበትና በምክክር ጉባዔው ላይ እንዲሳተፉ የማድረግ ቁልፍ ጉዳይ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በተለያዩ ምክንያቶች ከመሳተፍ የታቀቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ ሂደቱ እንዲመጡ ለማድረግ ተጨማሪ ጥረቶችን ማድረግ ማስፈለጉንም አንስተዋል። በተጨማሪም መሳሪያ አንግበው የሚቀሳቀሱ ቡድኖችም ያሏቸውን አጀንዳዎች ወደ ምክክሩ አምጥተው መሳተፋቸው ለምክክሩ ሂደት ውጤታማነት ተጨማሪ አቅም በመሆኑ ልዩ ጥረት አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በመድረኩ የተገኙ የሃይማኖት ተቋማት አባቶች፣ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀይማኖት ተቋማት ጉባዔና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መፍትሔ በማፍለቅ ረገድ የካበተ ልምድ ያላቸው በመሆን ቀሪ ስራዎች እንዲሳኩ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥቅምት እና ሕዳር ወር 2018 ዓ.ም ያከናወኗቸው ተግባራት
Dec 2, 2025 144
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥቅምት እና ሕዳር ወር 2018 ዓ.ም ቁልፍ የሆኑ ተከታታይ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተግባራትን አከናውነዋል። በደቡብ አፍሪካ አዘጋጅነት ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ ምድር በተካሄደው የቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ በመታደም ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት አስገኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው ላይ መሳተፍ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ የአፍሪካን የጋራ ድምጽ ለማጉላት ያስቻለ ነበር። ይህም የአህጉሪቱ ተጽዕኖ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ እየጎለበተ መምጣቱን ያረጋግጣል። የመስኖ ልማት ፕሮጀክት እና የቱሪዝም ልማት እንቅስቃሴን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ በነበራቸው ጉብኝት የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክትን የሥራ ሁኔታ ገምግመዋል። ፕሮጀክቱ 870 ሄክታር ላይ ያረፈ ሲሆን፤ 17000 ሄክታር መሬት በመስኖ አቅርቦት ይሸፍናል ተብሎ ይጠበቃል። በጥቅሉ የመገጭ ግድብ በሚጠናቀቅበት ወቅት የአካባቢውን የግብርና ምርታማነት በመሠረቱ የሚያሳድግ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዚያው በጎንደር ከተማ ምልከታቸውን ሲቀጥሉ፥ ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የታደሰውን የፋሲል ጊቢ መርቀዋል። በግቢው የተከናወነው ሰፊ የእድሳት ሥራ በቅርስ ስፍራው ነባሩን ታሪክ በመጠበቅ ውበቱን እና ተደራሽነቱን በማሻሻል አዲስ እስትንፋስ የሰጠ ሆኗል። የእድሳት ሥራው የቤተመንግሥቱን የግንባታ መዋቅር መጠገን፣ የእግር መንገዶችን ማሻሻል፣ ቁልፍ የሆኑ ሕንፃዎችን ከዝግባ እና ዋንዛ በባሕላዊ ቁሳቁሶችን ተጠቅሞ በማደስ የስፍራውን ግለ ወጥ መልክ እና ባሕርይ ለመጠበቅ ተሰርቷል። ለጎብኝዎች ምቾት የተሰናዱ አገልግሎት መስጫዎችም ትርጉም ባለው ደረጃ ተሻሽለዋል። አዲስ የቱሪስት ማዕከልም ተከፍቷል። ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች፣ የተሻሻሉ የመብራት እና የደኅንነት ሥርዓቶችም ተሰናድተዋል። እንደ አፄ ፋሲል፣ አፄ ቀዳማዊ ዮሃንስ እና አፄ ቀዳማዊ ኢያሱ አቢያተ መንግሥት ብሎም ድልድዮች፣ መታጠቢያ ሥፍራዎች፣ ታሪካዊ በሮች ወዘተ በጥንቃቄ ታድሰዋል። በተጨማሪም ከ40,000 ስኴር ሜትር በላይ የአካባቢው ምድር የማስዋብ ሥራ ተሰርቷል። ይኸም ለጎብኝዎች ይበልጥ ሳቢ የሆነ ከባቢ ፈጥሯል። አጠቃላይ የእድሳት ሥራው ከአንድ አመት በታች የፈጀ ሲሆን የዚህን አስደናቂ የታሪክ እና የባሕል ሥፍራ ለረዥም ጊዜ ጠብቆ በሚያቆይ አኳኋን ተከናውኗል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎርጎራ ጣናነሽ ፪ የተሰኘችዉን ጀልባ ሥራ አስጀምረዋል። ከ180 ተጓዦች በላይ የማጓጓዝ አቅም ያላት ጣናነሽ ለጉብኝት፣ ለመዝናናት እና አስደማሚውን የጣና ሀይቅ የተፈጥሮ ከባቢ ለመጎብኘት ወደ ጎርጎራ ኤኮ ሎጅ የሚደረገውን ጉዞ የበለጠ ምቹ እያደረገችው ትገኛለች። በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በባህር ዳር ከተማ በነበራቸው ጉብኝት፥ የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየምን እንዲሁም ከተማዋን ለቱሪዝም ዘርፍ ምቹ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ተመልክተዋል። የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ባስቀመጠው ስታንዳርድ መሰረት ደረጃውን የማሻሻል ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ እንደሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተመልክተዋል። ስታዲየሙ 52 ሺህ ተመልካቾችን መያዝ የሚችል ሲሆን የወንበር መግጠምና የሳር ንጣፍ ስራዎች ተጠናቀዋል። የመብራት ዝርጋታን ጨምሮ ሌሎች የስታዲየም ውስጥ መሰረተ ልማቶችም በፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ። ከዚህ በተጨማሪ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን መሠረት በማድረግ በባህር ዳር ጣና ሀይቅ ዳርቻ እየተገነባ ያለው ፈለገ ጊዮን ሪዞርትን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተመለከቱ ሲሆን፤ ሪዞርቱ ወደ ስራ ሲገባ የከተማዋን ቱሪዝም ከማነቃቃት ባሻገር ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል የሚፈጥር ይሆናል ሲሉ በወቅቱ ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዚሁ ወር፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአማራ ክልላዊ መንግሥት ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር መቀመጫ የሆነችውን ከሚሴ ከተማን የጎበኙ ሲሆን፥ በከተማዋ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ በጅምር ደረጃ ያለ ቢሆንም የ1.3 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መንገድ እና የእግረኛ መንገድ ሥራዎች የሚመሰገኑ ናቸው ብለዋል። የኮሪደር ልማት ሥራ የሕዝባዊ ሥፍራዎችን ደረጃ ከፍ በማድረግ ዕሳቤ በሁሉም ደረጃ በመላው ኢትዮጵያ እየተተገበረ መሆኑን እንደሚያሳይም ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ ለሌማት ትሩፋት ሥራ አስተዋጽዖ እያበረከተ ያለውን የኤልፎራ አግሮ-ኢንዱስትሪ የተቀናጀ የግብርና ልማት ፋብሪካንም ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ እምርታ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት ዋና መስሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት መለወጡን ተከትሎ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስፍራው ተገኝተው እንቅስቃሴውን ተመልክተዋል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የግንባታ ለውጥ እና ዘመናዊ የመሥሪያ ሥፍራ ጥበብን በማሳየት ለሠራተኞቹ እጅግ ምቹ የሆነ ስፍራንም መፍጠር እንደቻለም በጉብኝታቸው ወቀት ገልጸዋል። ተቋሙ በአምስት አመታት ጊዜ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ሲሆን፥ በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል ብለዋል። በቅርቡ የተጀመረው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርት አፕ ማዕከል ዜጎች ሀሳብ ብቻ ይዘው በመምጣት ፕሮቶታይፕ ለመፍጠር፣ ለማባዛት ብሎም ከግሉ ዘርፍ ኢንቬስተሮች ጋር እንዲገናኙ እድል ያመቻቻል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እስከ አሁን 200 ሀሳብ ፈጣሪዎች በዚህ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዚሁም ወር ነው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 50ኛ መደበኛ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ የወሰነው፡፡ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በደቡብ አፍሪካ አዘጋጅነት በተካሄደው የቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያን ስትራቴጂካዊ ጥቅም የሚያጸኑ የሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ዲፕሎመሲያዊ ተግባራትን አሳክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው ዋዜማ የአስተናጋጇ ሀገር ፕሬዝደንት ከሆኑት ሲሪል ራማፎሳ ጋር ተገናኝተዋል። በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከጉባኤው ጎን ለጎን ከIMF ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጂኦርጂየቫ ጋር በአለም አቀፍ የኢኮኖሚ አዝማሚያዎች፣ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም እንዲሁም ዘላቂ እና አካታች እድገትን ለመደገፍ ትብብርን ለማጠናከር ስላሉ እድሎች ላይ ተወያይተዋል። እንዲሁም ከአዲሱ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝደንት ዶክተር ሲዲ ኡልድ ታህ ጋር ተገናኝተው፥ ባንኩ በመላው አፍሪካ አካታች እድገት እንዲኖር የሚያደርገውን ወሳኝ ሚና በሚያጠናክርበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል። በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከጉባኤው ጎን ለጎን በርከት ያሉ ሀገራት መሪዎችን አግኝተው በሁለትዮሽ እና ስትራቴጂካዊ ትብብር ላይ የተወያዩ ሲሆን፥ የአቡዳቢው ልዑል አልጋ ወራሽ፣ የቱርክዬው ፕሬዝደንት፣ የፊንላንዱ ፕሬዝደንት፣ የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት እና የጀርመኑ ቻንሰለር የሚጠቀሱ ናቸው። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም ከህንድ፣ ቬይትናም፣ ደቡብ ኮሪያ እና አውስትራሊያ መሪዎች ጋር ፍሬያማ ውይይት አካሂደዋል። እንዲሁም ከዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ከብራዚል ፕሬዝደንት፣ ከኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ከጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር እና ከኢንዶኔዥያ ምክትል ፕሬዝደንት ጋር መልካም ውይይት አድርገዋል። ውይይታቸውም የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራ ትብብርን፣ ቅድሚያ በሚሰጣቸው በንግድ እና በምግብ ሉዓላዊነት ላይ ባተኮረ የግብርና ማዘመን ሥራን እንዲሁም በኢኮኖሚ እና ዘላቂ የመሠረተ ልማት ጉዳዮችን ያካተተ ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከቡድን 20 ጉባኤ ጎን ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር የባለብዙ ወገን ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ብሎም እንደ የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራ፣ ሰላም እና ፀጥታ፣ ዘላቂ ልማት ያሉ የጋራ አለምአቀፋዊ ትኩረቶችን በሚጠናከሩበት መንገድ ላይ ተወያይተዋል። ኢትዮጵያ የCOP32 አስተናጋጅ ሀገር እንደመሆኗ ሊደረግ ስለሚችለው ድጋፍም ተወያይተዋል። እንዲሁም የኢትዮ-አውሮፓ ኅብረት ግንኙነት ለማላቅ ከአውሮፓ ኅብረት ምክርቤት ፕሬዝደንት አንቶኒዮ ኮስታ ጋር በተለያዩ ዘርፎች ትብብሮችን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። በተመሳሳይ የሁለትዮሽ ውይይት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከካፍ ፕሬዝደንት ከዶክተር ፓትሪስ ሞትሲፒ እና ከአለም ባንክ ፕሬዝደንት አጄይ ባንጋ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። ከማሌዢያ እና ሲንጋፖር መሪዎች ጋር የተደረገ ዲፕሎማሲያዊ ውይይት በዚሁ ህዳር ወር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የማሌዢያ ፌደሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂምን እና የሲንጋፖሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ይፋዊ የአቀባበል አድርገውላቸዋል። ሁለቱም ጉብኝቶች የችግኝ ተከላ ሥነ ሥርዓትን፣ የቤተ መንግሥት ሙዚየም ጉብኝቶችን እና የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያካተቱ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር በክህሎት ስልጠና እና በካርቦን ንግድ ላይ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። በተመሳሳይ ኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ደግሞ ቱሪዝምን፣ ጤናን፣ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት እና የከተማ ትብብርን የሚመለከቱ ሰነዶችን ተፈራርመዋል። እነዚህ ጉብኝቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ ከደቡብ ምሥራቅ እስያ ጋር እያደገ የመጣውን ትብብር አጉልተው አሳይተዋል። ለኮፕ 32 ዝግጅት የኢትዮጵያ መመረጥ ኮፕ 32 የኢትዮጵያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑትን ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስን ፕሬዝደንት አድርጎ መመደቡን ተከትሎ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በተገኙበት ቁልፍ የዝግጅት ተግባራትን ለማቀናጀት የሚያስችል የብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባ ተደርጓል። ስብሰባው ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ስታስተናግድ አካታች እና በሚገባ የተሰናዳ ጉባኤ እንድታሳካ ለማረጋገጥ መንግሥት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ነበር። በጥቅሉ በጥቅምት እና ሕዳር ወር 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶችን፣ የቱሪዝም ልማት ስራዎችን እና ኢትዮጵያ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ትግበራን ለማሳለጥ እንዲሁም ሀገሪቱን በዲፕሎማሲ ከፍ ለማድረግ የተከተሉት አመራር በውጤት የታጀበ ነበር። በወሩ መጨረሻም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ እዝ አዛዥ ጄነራል ዳግቪን አር ኤም አንደርሰንን አግኝተው በቀጠናዊ የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አመራሩ በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል
Dec 1, 2025 189
ሚዛን አማን፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በቤንች ሸኮ እና በወላይታ ዞኖች ያሉትን የልማት አቅሞች በመጠቀም የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋትና የመንግሥት ተግባራትን በቁርጠኝነት ማከናወን ከአመራሩ እንደሚጠበቅ ተገለጸ። "በመደመር መንግሥት ዕይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ በዞኑ ሚዛን አማን ከተማ አጠቃላይ የአመራር ሥልጠና መስጠት ተጀምሯል። በመድረኩ ላይ መልእክት ያስተላለፉት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ ኩድን እንዳሉት፤ የብልጽግና ጉዞ በኅብረተሰቡ ሕይወት ውስጥ ውጤት እያመጣ እንዲቀጥል ብቃት ያለው አመራር መፍጠር ያስፈልጋል። በተለይ የአካባቢ ጸጋን መለየትና የመልማት ዕድልን ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ቁመና ላይ መገኘት ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ ነው ብለዋል። ለዚህም ፓርቲው የተለያዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን እየሰጠ ሲሆን አሁን ላይ የሚሰጠው ሥልጠና ልማትና የተግባር ውጤታማነት ላይ ያተኮረ መሆኑን ተናግረዋል። ዞኑ ለአግሮ ኢንዱስትሪ ያለው ምቹ ሁኔታ ትርጉም እንዲኖረው የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማስፋፋትና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ተግባርን በስኬት መምራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በተለይም በዞኑ ያለውን የልማት አቅም በመጠቀም የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት ከአመራሩ ይጠበቃል ብለዋል። በተመሳሳይም በወላይታ ዞን "በመደመር መንግስት እይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የ3ኛ ዙር የአመራሮች ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በመድረኩ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ፤በዞኑ በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ እመርታዊ ለውጦችን ለማስቀጠል የአመራሩን አቅም ማጎልበትና ብቁ አመራር መፍጠር እንደሚገባ ተናግረዋል። በግብርናና በገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት እና በኢንዱስትሪ አመርቂ ውጤት ለማስመዝገብና ዕድገቱን ለማስቀጠል በአመራሩ መካከል የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት ሊኖር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ትርክትን በማስረጽ ህዝቡ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በቅርበት ተከታትሎ ለመመለስ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም በአጽንኦት ተናግረዋል። በሥልጠናውም ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የተወጣጡ ከአንድ ሺህ 100 በላይ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ ሀገር በመገንባት ሂደት አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት ይገባል
Dec 1, 2025 161
ነቀምቴ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ ሀገር እንዲገነባ አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ተመለከተ። 20ኛው የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በነቀምቴ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ በፓናል ውይይቱ ላይ እንዳሉት፤ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር ወሳኝ ነው። ብሔሮችና ብሔረሰቦች በአንድነት የሚኖሩባት ነቀምቴ በነዋሪዎቿ ተሳትፎ በከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የልማት እቅዶችም በታቀዱት መሰረት እየተተገበሩ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም የከተማው ነዋሪ አንድነቱን አጠናክሮ የአካባቢውን ሰላም እንዲጠብቅና የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ እንዲያስቀጥል የተናገሩት ከንቲባው በተለይም ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ አገር እንዲገነባ አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የነቀምቴ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ መሰረት ሀይሉ በበኩላቸው፤ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር በህዝቦች መካከል ፍቅርና መከባበርን በማጎልበት ሕብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጠናከር የጎላ ሚና አለው ብለዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በነቀምቴ ከተማ መከበሩም የህዝቡን የእርስበርስ ትስስር የሚያጠናክር መሆኑንም አስረድተዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የነቀምቴ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ መላኩ ጌታሁን በበኩላቸው፤ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክሩ እሴቶች ላይ በትኩረት በመስራት ለሀገር እድገት መረባረብ ይገባል ብለዋል። የበለፀገች ሀገርን ለቀጣይ ትውልድ ለማውረስ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ሳይደናቀፉ መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተው የከተማው ነዋሪ ሰላሙን መጠበቅ እና አንድነቱን ማጠናከር እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አዘጋጅነት በሆሳዕና ከተማ እንደሚከበር ይታወቃል።
በዓሉ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ አበርክቷል - አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር
Dec 1, 2025 170
ቡሌ ሆራ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል መከበር ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ አበርክቷል ሲሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በምዕራብ ጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ ከተማ በድምቀት ተከብሯል። በበዓሉ አከባበር ላይ የተገኙት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በወቅቱ እንዳመለከቱት፤ በዓሉ ኢትዮጵያውያን በጋራ ለመኖር የተስማሙበትና በየዓመቱ ባሕላዊ እሴቶቻቸውን በአደባባይ የሚያንጽባርቁበት ነው። ይህም ጠንካራ የፌዴራል ስርዓት እንዲኖር በማድረግ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን እያጠናከረ ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ ማበርከቱን ተናግረዋል። በዓሉ የእርስ በእርስ ትስስርን በሚያጠናክር መልኩ በየደረጃው ተከብሮ ሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሀገር ደረጃ እንደሚከበር አንስተዋል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን በበኩላቸው፤ በዓሉ በክልሉ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና ትስስር በሚያጠናክር መልኩ ሲከበር ቆይቶ ዛሬ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በዓሉ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ባሕልና እሴቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ ሕብረ ብሔራዊ አንድነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ቃላቸውን የሚያድሱበት መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይ በዓሉ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ ሌሎች በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅት መከበሩ ለሀገራዊ ልማት በጋራ በመቆም ዳግም ሕብረት የሚጠናከርበት ነው ብለዋል። የምዕራብ ጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዱላ ህርባዬ፣ በዞኑ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ያሉትን ፀጋዎች ወደ ልማት በመለወጥ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። በተለይ ቡናን ጨምሮ ሌሎች የቅባት እህሎች እንዲሁም በቁም እንስሳት ምርታማነት ውጤታማ ያደረጉ ተግባራት በዞኑ መከናወናቸውን አንስተዋል። በዓሉ በክልል ደረጃ በዞኑ መከበሩ የአካባቢውን ጸጋ ከማስተዋወቅ ባለፈ የተጀመሩ ልማቶችን ለማጠናከር ድርሻው የጎላ ነው ብለዋል።
ፖለቲካ
በምስራቅ ጎጃም ዞን ሰላምን በማጽናትና ልማትን በማረጋገጥ በህዝቡ የታየው ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Dec 2, 2025 147
ደብረ ማርቆስ፤ ህዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ሰላምን በማጽናትና ልማትን በማረጋገጥ ረገድ በህዝቡ ዘንድ የታየው እገዛና ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ በሰላምና በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በደብረ ማርቆስ ከተማ ከነዋሪዎችና ከተለያዩ የህብረተሰቡ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በክልሉ የጥፋት ተልእኮ በመያዝ ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር፣ የልማት ስራዎች እንዳይሳኩና ማህበራዊ አገልግሎቶች እንዲስተጓጎሉ ፅንፈኞች ጥረት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የጽንፈኛ ቡድኑ የጥፋት ተልእኮ ግን በህዝቡ ጠንካራ ትብብርና በጸጥታ ኃይሉ ህግ የማስከበር እንቅስቃሴ በሁሉም አካባቢዎች ሰላምና መረጋጋት ማስፈን ተችሏል ብለዋል። ለዚህም የህዝቡ ትብብር፣ እገዛና ጽኑ የሰላም ፍላጎት ታክሎበት ችግሩን መፍታት ስለመቻሉ አንስተው ሰላምን በማጽናትና ልማትን በማረጋገጥ ረገድ የህዝቡ እገዛና ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢዎች ያለውን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል መንግስት እየሰራ መሆኑን ገልጸው የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ በማቋቋም ሰላማዊ ህይወት እንዲመሩ እየተደረገ ነው ብለዋል። አሁንም ቢሆን በጫካ የሚገኙ የታጠቁ ቡድኖች የሰላም እድሉን ከተጠቀሙ ምንጊዜም በሩ ክፍት ስለመሆኑ አረጋግጠዋል። ከዚህ ባለፈ ግን ሰላምን የማስጠበቅና ልማትን የማረጋገጥ ስራ በተቀናጀና በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ፤ ከነዋሪዎች ጋር በመተባበር በተሰራው ስራ የከተማዋ ሰላም በመልካም ሁኔታ ላይ እንዲገኝ አስችሏል ብለዋል። የዚህ መድረክ ዓላማም የተገኘውን ሰላም ማጽናትና የተጀመሩ የልማት ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል መሆኑን ገልጸዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ እስራኤል እምባቆም እና ወይዘሮ መስከረም ታደገ፤ የሰላም ጉዳይ በጋራ አቋም ይዘን የምንሰራበት በመሆኑ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ተሳትፈዋል።
የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል- የቀድሞ ታጣቂዎች
Dec 2, 2025 141
ገንዳ ውሃ ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ የተሳሳተ መንገድ ተከትለው በፈፀሙት ጥፋት በመፀፀት የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ መዘጋጀታቸውን በምዕራብ ጎንደር ዞን የሰላም አማራጭ ተቀብለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች ተናገሩ። በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ በዳንስ ጉንዶ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተቀብለው በመመለስ ሙሉ ትጥቃቸውን ለመንግስት አስረክበዋል። ከእነዚህም መካከል መብራቱ አወቀ በሰጠው አስተያየት፤ በተሳሳተ መንገድ ለጥፋት በመንቀሳቀስ ሕዝቡንና አካባቢውን ለችግር በማጋላጣቸው መፀፀቱን ተናግሯል። ችግርን በሰላማዊ ውይይት መፍታት ሲገባ ግጭት በመቀስቀስ ጥፋት መፈፀም ተገቢነት እንደሌለው በመገንዘብ የሰላም አማራጭ መቀበላቸውን አመልክቶ፤ የተሳሳተ መንገድ ተከትለን በፈፀምነው ጥፋት ተፀፅተን የበደልነውን ሕዝብ ለመካስ ተዘጋጅተናል ብሏል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል አብረውት ከነበሩት ጋር መመለሳቸውን የገለጸው ደግሞ ሌላው የቀድሞ ታጣቂ አየነው ውበት ነው። የተሳሳተ መንገድ በመከተል ሕዝባችንን ለችግር ዳርገናል ፤ በዚህ በመፀፀት የበደልነውን ሕዝብ በልማት ለመካስ ተዘጋጅተናል ሲል ገልጿል። የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ እንደገለጹት፤ የዞኑን ብሎም የክልሉን ሰላም ለማፅናት በቁርጠኝነት እየተሰራ ነው። መንግስት የሰጣቸውን የሰላም እድል እንዲጠቀሙ በተደረገው ጥረት የሰላም አማራጭን በመቀበል ቀደም ሲል የተመለሱ የተሃድሶ ስልጠና ተሰጥቷቸው ህይወታቸውን እየለወጡ መሆኑን አስረድተዋል። አሁንም የሰላም አምባሳደር ሆነው የመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችን የዞኑ መስተዳድርና ሕዝብ አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት በፈለጉት የሙያ መስክ እንዲሰማሩ ይደረጋል ብለዋል። በመከላከያ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ የ504ኛ ኮር ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ቾቤ ወርቁ በበኩላቸው፤ መንግስት ለሰላም ሁሌም በሩ ክፍት ነው ብለዋል። ሕብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት መረጃ በመስጠትና ችግር ወስጥ የገቡትን ወደ ሰላም እንዲመጡ በማድረግ እያበረከተ ላለው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበው ፤ በቀጣይም ይህ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።
ኮሚሽኑ የምክክር ጉባዔው የሚመክርባቸውን አጀንዳዎች ቀርጾ ይፋ ማድረግና ጉባዔውን ለመጥራት ዝግጅቱን እያጠናቀቀ ነው
Dec 2, 2025 194
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የምክክር ጉባዔው የሚመክርባቸውን አጀንዳዎች ቀርጾ ይፋ ማድረግና ጉባዔውን ለመጥራት ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ። ወደዚሁ ወሳኝ ምዕራፍ ለመሸጋገር መከናወን ያለባቸው ወሳኝ ቀሪ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ''የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማትና የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ተሳትፎ ለሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት'' በሚል መሪ ሃሳብ የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኮሚሽኑ ምክክሩ ሁሉን አሳታፊና አካታች ለማድረግ ለተሳታፊ ልየታ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል፡፡ የኅብረተሰብ ክፍሎችን፣የሃይማኖት እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ጨምሮ በርካታ ተቋማትና ማህበራትን፣ ታዋቂ ሰዎችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲሁም መንግሥትን በተወካዮቻቸው አማካኝነት ማካተትና ማሳተፍ መቻሉም ገልጸዋል። በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይወሰንም የዳያስፖራ ወገኖችም በሂደቱ እንዲሳተፉ ጥረት መደረጉን አንስተዋል። ኮሚሽኑ አሁን ላይ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው የሚመክርባቸውን አጀንዳዎች ቀርጾ ይፋ ማድረግና ጉባዔውን ለመጥራት ጫፍ ላይ መድረሱን አስታውቀው፤ ለዚህም ቅድመ ዝግጅቶችን እያደረገ እንደሚገኝ አመላክተዋል። ወደዚሁ ወሳኝ ምዕራፍ ለመሸጋገር መከናወን ያለባቸው ወሳኝ ቀሪ ተግባራት አሉ ያሉት ዋና ኮሚሽነሩ፤ የትግራይ ክልል ሕዝብና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አጀንዳቸውን የሚሰጡበትና በምክክር ጉባዔው ላይ እንዲሳተፉ የማድረግ ቁልፍ ጉዳይ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በተለያዩ ምክንያቶች ከመሳተፍ የታቀቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ ሂደቱ እንዲመጡ ለማድረግ ተጨማሪ ጥረቶችን ማድረግ ማስፈለጉንም አንስተዋል። በተጨማሪም መሳሪያ አንግበው የሚቀሳቀሱ ቡድኖችም ያሏቸውን አጀንዳዎች ወደ ምክክሩ አምጥተው መሳተፋቸው ለምክክሩ ሂደት ውጤታማነት ተጨማሪ አቅም በመሆኑ ልዩ ጥረት አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በመድረኩ የተገኙ የሃይማኖት ተቋማት አባቶች፣ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀይማኖት ተቋማት ጉባዔና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መፍትሔ በማፍለቅ ረገድ የካበተ ልምድ ያላቸው በመሆን ቀሪ ስራዎች እንዲሳኩ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥቅምት እና ሕዳር ወር 2018 ዓ.ም ያከናወኗቸው ተግባራት
Dec 2, 2025 144
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥቅምት እና ሕዳር ወር 2018 ዓ.ም ቁልፍ የሆኑ ተከታታይ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተግባራትን አከናውነዋል። በደቡብ አፍሪካ አዘጋጅነት ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ ምድር በተካሄደው የቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ በመታደም ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት አስገኝተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው ላይ መሳተፍ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ የአፍሪካን የጋራ ድምጽ ለማጉላት ያስቻለ ነበር። ይህም የአህጉሪቱ ተጽዕኖ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ እየጎለበተ መምጣቱን ያረጋግጣል። የመስኖ ልማት ፕሮጀክት እና የቱሪዝም ልማት እንቅስቃሴን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ በነበራቸው ጉብኝት የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክትን የሥራ ሁኔታ ገምግመዋል። ፕሮጀክቱ 870 ሄክታር ላይ ያረፈ ሲሆን፤ 17000 ሄክታር መሬት በመስኖ አቅርቦት ይሸፍናል ተብሎ ይጠበቃል። በጥቅሉ የመገጭ ግድብ በሚጠናቀቅበት ወቅት የአካባቢውን የግብርና ምርታማነት በመሠረቱ የሚያሳድግ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዚያው በጎንደር ከተማ ምልከታቸውን ሲቀጥሉ፥ ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የታደሰውን የፋሲል ጊቢ መርቀዋል። በግቢው የተከናወነው ሰፊ የእድሳት ሥራ በቅርስ ስፍራው ነባሩን ታሪክ በመጠበቅ ውበቱን እና ተደራሽነቱን በማሻሻል አዲስ እስትንፋስ የሰጠ ሆኗል። የእድሳት ሥራው የቤተመንግሥቱን የግንባታ መዋቅር መጠገን፣ የእግር መንገዶችን ማሻሻል፣ ቁልፍ የሆኑ ሕንፃዎችን ከዝግባ እና ዋንዛ በባሕላዊ ቁሳቁሶችን ተጠቅሞ በማደስ የስፍራውን ግለ ወጥ መልክ እና ባሕርይ ለመጠበቅ ተሰርቷል። ለጎብኝዎች ምቾት የተሰናዱ አገልግሎት መስጫዎችም ትርጉም ባለው ደረጃ ተሻሽለዋል። አዲስ የቱሪስት ማዕከልም ተከፍቷል። ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች፣ የተሻሻሉ የመብራት እና የደኅንነት ሥርዓቶችም ተሰናድተዋል። እንደ አፄ ፋሲል፣ አፄ ቀዳማዊ ዮሃንስ እና አፄ ቀዳማዊ ኢያሱ አቢያተ መንግሥት ብሎም ድልድዮች፣ መታጠቢያ ሥፍራዎች፣ ታሪካዊ በሮች ወዘተ በጥንቃቄ ታድሰዋል። በተጨማሪም ከ40,000 ስኴር ሜትር በላይ የአካባቢው ምድር የማስዋብ ሥራ ተሰርቷል። ይኸም ለጎብኝዎች ይበልጥ ሳቢ የሆነ ከባቢ ፈጥሯል። አጠቃላይ የእድሳት ሥራው ከአንድ አመት በታች የፈጀ ሲሆን የዚህን አስደናቂ የታሪክ እና የባሕል ሥፍራ ለረዥም ጊዜ ጠብቆ በሚያቆይ አኳኋን ተከናውኗል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎርጎራ ጣናነሽ ፪ የተሰኘችዉን ጀልባ ሥራ አስጀምረዋል። ከ180 ተጓዦች በላይ የማጓጓዝ አቅም ያላት ጣናነሽ ለጉብኝት፣ ለመዝናናት እና አስደማሚውን የጣና ሀይቅ የተፈጥሮ ከባቢ ለመጎብኘት ወደ ጎርጎራ ኤኮ ሎጅ የሚደረገውን ጉዞ የበለጠ ምቹ እያደረገችው ትገኛለች። በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በባህር ዳር ከተማ በነበራቸው ጉብኝት፥ የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየምን እንዲሁም ከተማዋን ለቱሪዝም ዘርፍ ምቹ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ተመልክተዋል። የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ባስቀመጠው ስታንዳርድ መሰረት ደረጃውን የማሻሻል ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ እንደሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተመልክተዋል። ስታዲየሙ 52 ሺህ ተመልካቾችን መያዝ የሚችል ሲሆን የወንበር መግጠምና የሳር ንጣፍ ስራዎች ተጠናቀዋል። የመብራት ዝርጋታን ጨምሮ ሌሎች የስታዲየም ውስጥ መሰረተ ልማቶችም በፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ። ከዚህ በተጨማሪ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን መሠረት በማድረግ በባህር ዳር ጣና ሀይቅ ዳርቻ እየተገነባ ያለው ፈለገ ጊዮን ሪዞርትን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተመለከቱ ሲሆን፤ ሪዞርቱ ወደ ስራ ሲገባ የከተማዋን ቱሪዝም ከማነቃቃት ባሻገር ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል የሚፈጥር ይሆናል ሲሉ በወቅቱ ተናግረዋል። በሌላ በኩል በዚሁ ወር፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአማራ ክልላዊ መንግሥት ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር መቀመጫ የሆነችውን ከሚሴ ከተማን የጎበኙ ሲሆን፥ በከተማዋ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ በጅምር ደረጃ ያለ ቢሆንም የ1.3 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መንገድ እና የእግረኛ መንገድ ሥራዎች የሚመሰገኑ ናቸው ብለዋል። የኮሪደር ልማት ሥራ የሕዝባዊ ሥፍራዎችን ደረጃ ከፍ በማድረግ ዕሳቤ በሁሉም ደረጃ በመላው ኢትዮጵያ እየተተገበረ መሆኑን እንደሚያሳይም ገልጸዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ ለሌማት ትሩፋት ሥራ አስተዋጽዖ እያበረከተ ያለውን የኤልፎራ አግሮ-ኢንዱስትሪ የተቀናጀ የግብርና ልማት ፋብሪካንም ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ እምርታ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት ዋና መስሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት መለወጡን ተከትሎ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስፍራው ተገኝተው እንቅስቃሴውን ተመልክተዋል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የግንባታ ለውጥ እና ዘመናዊ የመሥሪያ ሥፍራ ጥበብን በማሳየት ለሠራተኞቹ እጅግ ምቹ የሆነ ስፍራንም መፍጠር እንደቻለም በጉብኝታቸው ወቀት ገልጸዋል። ተቋሙ በአምስት አመታት ጊዜ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ሲሆን፥ በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል ብለዋል። በቅርቡ የተጀመረው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርት አፕ ማዕከል ዜጎች ሀሳብ ብቻ ይዘው በመምጣት ፕሮቶታይፕ ለመፍጠር፣ ለማባዛት ብሎም ከግሉ ዘርፍ ኢንቬስተሮች ጋር እንዲገናኙ እድል ያመቻቻል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እስከ አሁን 200 ሀሳብ ፈጣሪዎች በዚህ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል። በዚሁም ወር ነው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 50ኛ መደበኛ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ የወሰነው፡፡ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በደቡብ አፍሪካ አዘጋጅነት በተካሄደው የቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያን ስትራቴጂካዊ ጥቅም የሚያጸኑ የሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ዲፕሎመሲያዊ ተግባራትን አሳክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው ዋዜማ የአስተናጋጇ ሀገር ፕሬዝደንት ከሆኑት ሲሪል ራማፎሳ ጋር ተገናኝተዋል። በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከጉባኤው ጎን ለጎን ከIMF ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጂኦርጂየቫ ጋር በአለም አቀፍ የኢኮኖሚ አዝማሚያዎች፣ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም እንዲሁም ዘላቂ እና አካታች እድገትን ለመደገፍ ትብብርን ለማጠናከር ስላሉ እድሎች ላይ ተወያይተዋል። እንዲሁም ከአዲሱ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝደንት ዶክተር ሲዲ ኡልድ ታህ ጋር ተገናኝተው፥ ባንኩ በመላው አፍሪካ አካታች እድገት እንዲኖር የሚያደርገውን ወሳኝ ሚና በሚያጠናክርበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል። በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከጉባኤው ጎን ለጎን በርከት ያሉ ሀገራት መሪዎችን አግኝተው በሁለትዮሽ እና ስትራቴጂካዊ ትብብር ላይ የተወያዩ ሲሆን፥ የአቡዳቢው ልዑል አልጋ ወራሽ፣ የቱርክዬው ፕሬዝደንት፣ የፊንላንዱ ፕሬዝደንት፣ የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት እና የጀርመኑ ቻንሰለር የሚጠቀሱ ናቸው። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም ከህንድ፣ ቬይትናም፣ ደቡብ ኮሪያ እና አውስትራሊያ መሪዎች ጋር ፍሬያማ ውይይት አካሂደዋል። እንዲሁም ከዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ከብራዚል ፕሬዝደንት፣ ከኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ከጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር እና ከኢንዶኔዥያ ምክትል ፕሬዝደንት ጋር መልካም ውይይት አድርገዋል። ውይይታቸውም የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራ ትብብርን፣ ቅድሚያ በሚሰጣቸው በንግድ እና በምግብ ሉዓላዊነት ላይ ባተኮረ የግብርና ማዘመን ሥራን እንዲሁም በኢኮኖሚ እና ዘላቂ የመሠረተ ልማት ጉዳዮችን ያካተተ ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከቡድን 20 ጉባኤ ጎን ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር የባለብዙ ወገን ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ብሎም እንደ የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራ፣ ሰላም እና ፀጥታ፣ ዘላቂ ልማት ያሉ የጋራ አለምአቀፋዊ ትኩረቶችን በሚጠናከሩበት መንገድ ላይ ተወያይተዋል። ኢትዮጵያ የCOP32 አስተናጋጅ ሀገር እንደመሆኗ ሊደረግ ስለሚችለው ድጋፍም ተወያይተዋል። እንዲሁም የኢትዮ-አውሮፓ ኅብረት ግንኙነት ለማላቅ ከአውሮፓ ኅብረት ምክርቤት ፕሬዝደንት አንቶኒዮ ኮስታ ጋር በተለያዩ ዘርፎች ትብብሮችን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። በተመሳሳይ የሁለትዮሽ ውይይት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከካፍ ፕሬዝደንት ከዶክተር ፓትሪስ ሞትሲፒ እና ከአለም ባንክ ፕሬዝደንት አጄይ ባንጋ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። ከማሌዢያ እና ሲንጋፖር መሪዎች ጋር የተደረገ ዲፕሎማሲያዊ ውይይት በዚሁ ህዳር ወር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የማሌዢያ ፌደሬሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂምን እና የሲንጋፖሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ይፋዊ የአቀባበል አድርገውላቸዋል። ሁለቱም ጉብኝቶች የችግኝ ተከላ ሥነ ሥርዓትን፣ የቤተ መንግሥት ሙዚየም ጉብኝቶችን እና የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያካተቱ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር በክህሎት ስልጠና እና በካርቦን ንግድ ላይ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። በተመሳሳይ ኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ደግሞ ቱሪዝምን፣ ጤናን፣ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት እና የከተማ ትብብርን የሚመለከቱ ሰነዶችን ተፈራርመዋል። እነዚህ ጉብኝቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ ከደቡብ ምሥራቅ እስያ ጋር እያደገ የመጣውን ትብብር አጉልተው አሳይተዋል። ለኮፕ 32 ዝግጅት የኢትዮጵያ መመረጥ ኮፕ 32 የኢትዮጵያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑትን ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስን ፕሬዝደንት አድርጎ መመደቡን ተከትሎ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በተገኙበት ቁልፍ የዝግጅት ተግባራትን ለማቀናጀት የሚያስችል የብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባ ተደርጓል። ስብሰባው ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ስታስተናግድ አካታች እና በሚገባ የተሰናዳ ጉባኤ እንድታሳካ ለማረጋገጥ መንግሥት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ነበር። በጥቅሉ በጥቅምት እና ሕዳር ወር 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶችን፣ የቱሪዝም ልማት ስራዎችን እና ኢትዮጵያ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ትግበራን ለማሳለጥ እንዲሁም ሀገሪቱን በዲፕሎማሲ ከፍ ለማድረግ የተከተሉት አመራር በውጤት የታጀበ ነበር። በወሩ መጨረሻም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ እዝ አዛዥ ጄነራል ዳግቪን አር ኤም አንደርሰንን አግኝተው በቀጠናዊ የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አመራሩ በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል
Dec 1, 2025 189
ሚዛን አማን፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በቤንች ሸኮ እና በወላይታ ዞኖች ያሉትን የልማት አቅሞች በመጠቀም የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋትና የመንግሥት ተግባራትን በቁርጠኝነት ማከናወን ከአመራሩ እንደሚጠበቅ ተገለጸ። "በመደመር መንግሥት ዕይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ በዞኑ ሚዛን አማን ከተማ አጠቃላይ የአመራር ሥልጠና መስጠት ተጀምሯል። በመድረኩ ላይ መልእክት ያስተላለፉት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ ኩድን እንዳሉት፤ የብልጽግና ጉዞ በኅብረተሰቡ ሕይወት ውስጥ ውጤት እያመጣ እንዲቀጥል ብቃት ያለው አመራር መፍጠር ያስፈልጋል። በተለይ የአካባቢ ጸጋን መለየትና የመልማት ዕድልን ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ቁመና ላይ መገኘት ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ ነው ብለዋል። ለዚህም ፓርቲው የተለያዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን እየሰጠ ሲሆን አሁን ላይ የሚሰጠው ሥልጠና ልማትና የተግባር ውጤታማነት ላይ ያተኮረ መሆኑን ተናግረዋል። ዞኑ ለአግሮ ኢንዱስትሪ ያለው ምቹ ሁኔታ ትርጉም እንዲኖረው የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማስፋፋትና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ተግባርን በስኬት መምራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በተለይም በዞኑ ያለውን የልማት አቅም በመጠቀም የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት ከአመራሩ ይጠበቃል ብለዋል። በተመሳሳይም በወላይታ ዞን "በመደመር መንግስት እይታ፤ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የ3ኛ ዙር የአመራሮች ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በመድረኩ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ፤በዞኑ በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ እመርታዊ ለውጦችን ለማስቀጠል የአመራሩን አቅም ማጎልበትና ብቁ አመራር መፍጠር እንደሚገባ ተናግረዋል። በግብርናና በገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት እና በኢንዱስትሪ አመርቂ ውጤት ለማስመዝገብና ዕድገቱን ለማስቀጠል በአመራሩ መካከል የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት ሊኖር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ትርክትን በማስረጽ ህዝቡ የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በቅርበት ተከታትሎ ለመመለስ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም በአጽንኦት ተናግረዋል። በሥልጠናውም ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የተወጣጡ ከአንድ ሺህ 100 በላይ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ ሀገር በመገንባት ሂደት አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት ይገባል
Dec 1, 2025 161
ነቀምቴ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ ሀገር እንዲገነባ አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ተመለከተ። 20ኛው የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በነቀምቴ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ በፓናል ውይይቱ ላይ እንዳሉት፤ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር ወሳኝ ነው። ብሔሮችና ብሔረሰቦች በአንድነት የሚኖሩባት ነቀምቴ በነዋሪዎቿ ተሳትፎ በከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የልማት እቅዶችም በታቀዱት መሰረት እየተተገበሩ መሆኑን አንስተዋል። በቀጣይም የከተማው ነዋሪ አንድነቱን አጠናክሮ የአካባቢውን ሰላም እንዲጠብቅና የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ እንዲያስቀጥል የተናገሩት ከንቲባው በተለይም ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ አገር እንዲገነባ አሰባሳቢ ትርክት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የነቀምቴ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ መሰረት ሀይሉ በበኩላቸው፤ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር በህዝቦች መካከል ፍቅርና መከባበርን በማጎልበት ሕብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጠናከር የጎላ ሚና አለው ብለዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በነቀምቴ ከተማ መከበሩም የህዝቡን የእርስበርስ ትስስር የሚያጠናክር መሆኑንም አስረድተዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የነቀምቴ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ መላኩ ጌታሁን በበኩላቸው፤ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክሩ እሴቶች ላይ በትኩረት በመስራት ለሀገር እድገት መረባረብ ይገባል ብለዋል። የበለፀገች ሀገርን ለቀጣይ ትውልድ ለማውረስ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ሳይደናቀፉ መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተው የከተማው ነዋሪ ሰላሙን መጠበቅ እና አንድነቱን ማጠናከር እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አዘጋጅነት በሆሳዕና ከተማ እንደሚከበር ይታወቃል።
በዓሉ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ አበርክቷል - አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር
Dec 1, 2025 170
ቡሌ ሆራ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡- የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል መከበር ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ አበርክቷል ሲሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በምዕራብ ጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ ከተማ በድምቀት ተከብሯል። በበዓሉ አከባበር ላይ የተገኙት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በወቅቱ እንዳመለከቱት፤ በዓሉ ኢትዮጵያውያን በጋራ ለመኖር የተስማሙበትና በየዓመቱ ባሕላዊ እሴቶቻቸውን በአደባባይ የሚያንጽባርቁበት ነው። ይህም ጠንካራ የፌዴራል ስርዓት እንዲኖር በማድረግ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን እያጠናከረ ለሀገር ገጽታ ግንባታ የላቀ አስተዋጾ ማበርከቱን ተናግረዋል። በዓሉ የእርስ በእርስ ትስስርን በሚያጠናክር መልኩ በየደረጃው ተከብሮ ሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሀገር ደረጃ እንደሚከበር አንስተዋል። የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን በበኩላቸው፤ በዓሉ በክልሉ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና ትስስር በሚያጠናክር መልኩ ሲከበር ቆይቶ ዛሬ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በዓሉ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ባሕልና እሴቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ ሕብረ ብሔራዊ አንድነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ቃላቸውን የሚያድሱበት መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይ በዓሉ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ ሌሎች በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅት መከበሩ ለሀገራዊ ልማት በጋራ በመቆም ዳግም ሕብረት የሚጠናከርበት ነው ብለዋል። የምዕራብ ጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዱላ ህርባዬ፣ በዞኑ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ያሉትን ፀጋዎች ወደ ልማት በመለወጥ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። በተለይ ቡናን ጨምሮ ሌሎች የቅባት እህሎች እንዲሁም በቁም እንስሳት ምርታማነት ውጤታማ ያደረጉ ተግባራት በዞኑ መከናወናቸውን አንስተዋል። በዓሉ በክልል ደረጃ በዞኑ መከበሩ የአካባቢውን ጸጋ ከማስተዋወቅ ባለፈ የተጀመሩ ልማቶችን ለማጠናከር ድርሻው የጎላ ነው ብለዋል።
ማህበራዊ
ጎንደር ዩንቨርሲቲ ሙስናን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በምርምርና አሰራር በመደገፍ የድርሻውን እየተወጣ ነው
Dec 2, 2025 68
ጎንደር፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፡- ጎንደር ዩንቨርሲቲ የሙስና ወንጀሎችን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በምርምርና አሰራር በመደገፍ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገለጸ። ዩንቨርሲቲው "ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር’’ በሚል መሪ ሀሳብ 22ኛውን የዓለም የፀረ ሙስና ቀን በፓናል ውይይት አክብሯል፡፡ በዚህ ወቅት የዩንቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስራት አጸደወይን(ዶ/ር)፤ የሀገርን የኢኮኖሚና የዜጎችም ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ላይ እንቅፋት የሆነውን ሙስና መከላከል ላይ በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ ሙስና የዘመናት ችግር ሆኖ የዘለቀ መሆኑን አንስተው፤ ከለውጡ ወዲህ መንግስት ለፀረ ሙስና ትግሉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሮ የአሰራርና የህግ ማእቀፎችን በማዘጋጀት የሙስና ወንጀል ፈጻሚዎች ለሕግ ቀርበው ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መንግስት ሙስናን የመከላከል ተግባርና ጥረት ውጤታማ እንዲሆን በምርምር በመደገፍ ረገድ ዩኒቨርሲቲው የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ከማቋቋም ጀምሮ በሰለጠነ የሰው ሃይልና በግብአት በማጠናከር ለሙስና የተጋለጡ አሰራሮችን ከሰው ንክኪ ነፃ የሆኑ አሰራር ማመቻቸቱንም አንስተዋል፡፡ ለሙስና ተጋላጭ የሆኑ የስራ ክፍሎችን በመለየት አሰራሮችን የመፈተሸና የመከታተል ስራዎች እየተካሄደ ነው ያሉት የዩኒቨርሲቲው የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ወይዘሮ ንግስት መኮንን ናቸው፡፡ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር ከመዘርጋት ጀምሮ ተቋሙን በአሰራርና በአደረጃጀት በማዘመን ቀልጣፋና ፍትሃዊ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲጠናከር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሙስናን መታገል የምርጫ ሳይሆን የሕልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ተማሪዎችን በስነ ምግባር ከማነጽ ጀምሮ በፀረ ሙስና ትግሉ የስነ ምግባር አምባሳደር በመሆን የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ በየደረጃው የሚገኙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ሰራተኞች በኦን ላይን የሀብት ማሳውቅና የማስመዝገብ ስራ እንዲያካሂዱ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ወደ ስራ መገባቱንም አንስተዋል፡፡ በፓናል ውይይት ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣መምህራን ፣ተማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡
የኃይማኖት ተቋማት ፍቅርን፣ ሰላምንና አብሮነትን ማስተማር ይጠበቅባቸዋል - ጉባኤው
Dec 2, 2025 56
ነቀምት፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ የኃይማኖት ተቋማት ከሁሉም ነገር በፊት ፍቅርን፣ ሰላምንና አብሮነትን ማስተማር እንደሚጠበቅባቸው የነቀምቴ ከተማ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ገለጸ። የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር በሰላምና ጸጥታ እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከሃይማኖት ተቋማት አባቶች ጋር ውይይት አካሂዷል። በመድረኩ የተገኙት የነቀምቴ ከተማ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢ ቄስ አስፋው ተረፍሳ፤ የኃይማኖት ተቋማት ዋነኛ ተግባር ፍቅርን፣ ሰላምንና መተሳሰብን በማስተማር ሰላምን ማጽናት መሆኑን አንስተው በዚህ ረገድ ተቋማቱ የመንግስትን ጥረት በማገዝ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል። ጉባኤው ከተቋቋመ ጀመሮ በዚህ ዙሪያ በስፋት እየሰራ መሆኑን አንስተው ይህንኑ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የምስራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅና የጉባኤው አባል ቄስ ገረመው በቀለ፤ በየቤተ እምነቱ የሚሰጡ አስተምህሮዎች ለሀገር ሰላምና ለትውልድ ግንባታ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ቀጣይነት ያለው ተግባር ከተቋማቱ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል። የነቀምቴ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ኃላፊ ሼህ ተማም ሞሀመድ፤ በበኩላቸው የእምነት ተቋሞቻችን ለሀገር ሰላምና ለትውልድ ግንባታ ትልቅ አበርክቶ አላቸው ብለዋል። በመሆኑም በየድርሻችን ሰላምን፣ ፍቅርንና አብሮነትን በማስተማር ከምንም በላይ ለሀገርና ለትውልድ ግንባታ አደራችንን ልንወጣ ይገባል ነው ያሉት። የኃይማኖት አባቶች እያደረጉት ባለው ያለሰለሰ ጥረትም በተለያዩ አካባቢዎች የሰፈነውን ሰላም በማዝለቅ የልማት ተግባራት እንዲጠናከሩ ትልቁን ድርሻ እየተወጡ መሆኑን ጠቅሰዋል። የሀይማኖት አባቶች ሰላምና አብሮነት ዙሪያ የሚያስተላልፉት አስተምህሮ ለሀገር ልማትና ዘላቂ ሰላም የራሱን ድርሻ እየተወጣ ነው ያሉት ደግሞ የነቀምቴ ከተማ ከንቲባ መሰረት ሀይሉ ናቸው። በዚህም በከተማዋ የሰፈነውን ሰላም በማዝለቅ የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ እንዲሳካ የኃይማኖት አባቶቹ እያከናወኑት ያለውን ተግባር አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል።
ምሁራን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ ሀሳቦችን በማፍለቅ ዘላቂ ሰላምን የማፅናት ሚናቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል
Dec 2, 2025 56
ደብረማርቆስ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፡- ምሁራን ሀገር አሻጋሪ እና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ ሃሳቦችን በማፍለቅ ዘላቂ ሰላምን የማፅናት ሚናቸውን ይበልጥ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ። የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) በወቅታዊና ሰላም ግንባታ ጉዳይ ዙሪያ ዛሬ ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር ተወያይተዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ዩኒቨርሲቲዎች ከመማር ማስተማር ስራቸው በተጓዳኝ ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሄዎችን የማቅረብ ሃላፊነት አለባቸው ብለዋል። በመሆኑም በተለይ ምሁራን ሀገር አሻጋሪ እና ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን አጠናካሪ ሃሳቦችን በማፍለቅ ዘላቂ ሰላምን ለማፅናት ሚናቸውን ይበልጥ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። ቸግሮች በሰላማዊ ውይይት እንዲፈቱ መንግስት በሆደ ሰፊነት ረጅም ርቀት በመሄድ ሲሰራ መቆየቱን አውስተው፤ይህንን ተግባር አሁንም አጠናክሮ መቀጠሉን አንስተዋል። የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሳይህ ካሳው(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ተቋሙ ሰላምን በመደገፍ የመማር ማስተማሩን ስራ ለማሳካት ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። የሰላም ጉዳይ የጋራ ስለሆነ በሕብረት መስራታችንን አጠናክረን መቀጠል ይገባናል ብለዋል። ሰላምን በዘላቂነት አፅንቶ ለማስቀጠል ሁላችንም የድርሻችንን መወጣት አለብን ያሉት ደግሞ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ ናቸው። ምሁራን እውቀታቸውን ለሰላም እና ለልማት ግንባታ በማዋል ድጋፋቸውን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸውም አመልክተዋል። ከውይይቱ ተሳታፊ ምሁራን መካከል የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ይኼይስ አረጉ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ መንግስት ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እያደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ የድርሻችንን መወጣት ይገባናል ብለዋል። የዩኒቨርሲቲው ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር በእውቀት ሲሳይ በበኩላቸው፤ ሰላምን ማፅናት የእያንዳንዳችንን ተሳትፎ የሚጠይቅ ስለሆነ ትኩረት ልንሰጠው ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
ለሀገራዊ ምክክሩ ቀጣይ ስራዎች የሀይማኖት ተቋማትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አስተዋጽኦ የበለጠ መጠናከር አለበት
Dec 2, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ ለሀገራዊ ምክክር ቀጣይ ስራዎች የሀይማኖት ተቋማትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ የበለጠ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታወቁ። ኮሚሽኑ ወደ ምክክር ሂደቱ ለመሸጋገር የሚያስችሉ ወሳኝ የሆኑ ቀሪ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፣ "የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማትና የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ተሳትፎ ለሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የምክክር መድረክ አካሄዷል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኮሚሽኑ ምክክሩ ሁሉን አሳታፊና አካታች እንዲሆን ለተሳታፊ ልየታ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ በዚህም የኅብረተሰብ ክፍሎችን፣ የሃይማኖት እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን፣ በርካታ ተቋማትና ማህበራትን፣ ታዋቂ ሰዎችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲሁም መንግሥትን በተወካዮቻቸው አማካኝነት ማካተትና ማሳተፍ መቻሉን ገልጸዋል። ኮሚሽኑ በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይወሰን ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በሂደቱ እንዲሳተፉ ጥረት ማድረጉን አንስተዋል። ኮሚሽኑ ጉባዔው የሚመክርባቸውን አጀንዳዎች ይፋ ለማድረግና ጉባዔውን ለመጥራት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን አስታውቀው፤ ለዚህም ዝግጅቶችን እያደረገ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ከፍተኛ አመራር አባለት፣ የሀይማኖት ተቋማት ጉባዔና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የካበተ ልምድ ስላላቸው ቀሪ ስራዎች እንዲሳኩ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክነት የህግ አገልግሎት መምሪያ ኃላፊ መምህር አባ ገብረሥላሴ ጌትነት እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ምክክር ለሀገር መንግስት ግንባታ ወሳኝ ጉዳይ ነው። ለምክክሩ ስኬታማነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ ዑስታዝ ተምኪን አብዱላሂ፤ ኮሚሽኑ ስኬታማ ስራ ማከናወኑን ተናግረው፤ ከዚህ በፊት ተሳትፎ ያላደረጉ አካላት እንዲሳተፉ የበኩላችንን ሃላፊነት እንወጣለን ብለዋል። በኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተክርስቲያናት ህብረት የአዲሰ አበባ የቦርድ ሰብሳቢ መጋቢ ሲሳይ መላኩ (ዶ/ር) ኮሚሽኑ እያከናወነ ያለው ስራ አበረታች መሆኑን አንስተው፤ ቀሪ ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ ትብብራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ተረፈ ደጌቲ በበኩላቸው፤ ኮሚሽኑ ያከናወናቸው ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ገልፀው፤ በቀጣይ የሚከናወኑ ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል።
ኢኮኖሚ
ብሔራዊ ባንክ ያካሄደው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ይፋ ሆነ
Dec 2, 2025 107
አዲስ አበባ፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ያካሄደውን የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ይፋ አድርጓል። በጨረታ ሂደቱ 17 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን በዚህም የምንዛሪ ጨረታ አንድ የአሜሪካን ዶላር ዋጋ በአማካኝ 154 ነጥብ 3993 ብር ሆኖ መመዝገቡ ተገልጿል፡፡ ቀጣዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።
በከተሞች መሰረተ ልማትን በማሟላት ለነዋሪዎች ምቹ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል - ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ
Dec 2, 2025 95
ከሚሴ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፡-በሀገሪቱ ከተሞች መሰረተ ልማትን በማሟላት ለነዋሪዎች እና ለኢንቨስትመንት ምቹ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ። ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እና ሌሎች የፌዴራል ከፍተኛ አመራሮች በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ከሚሴና ጨፋ ሮቢት ከተሞች የልማት ሥራ እንቅስቃሴዎችን ዛሬ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ሚኒሰትሯ እንዳመለከቱት፤ በከተሞች የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለያዩ የመሰረት ልማት ግንባታዎች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ። በሀገሪቱ ከተሞች መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ለነዋሪዎች እና ለኢንቨስትመንት ምቹ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የተጀመሩ የልማት ስራዎች አበረታች መሆናቸውንና ይበልጥ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል። የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው ፣ በዞኑ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው ብለዋል። በዞኑ ከተሞችም መሰረተ ልማትን በማሟላት ለነዋሪዎች፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በጉብኝቱም የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
የገጠር ትራንስፎርሜሽንን በቅንጅት ማሳለጥ የሚያስችል የ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቷል -ግብርና ሚኒስቴር
Dec 2, 2025 94
አዲስ አበባ፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ የገጠር ትራንስፎርሜሽንን በቅንጅት ማሳለጥ የሚያስችል የ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት "የገጠር ትራንስፎርሜሽንን በማሳደግ ውጤታማና ባለብዙ ዘርፍ የትብብር ተፅዕኖን ማጎልበት" በሚል ሀሳብ የፓናል ውይይት አካሂዷል። በፓናል ውይይቱ የተገኙት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር) የገጠር ሽግግርን ለማፋጠን ግብርናውን ከማዘመን ባሻገር ሌሎች ወሳኝ ሥራዎች መኖራቸውን ገልጸዋል። ግብርናውን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር በተጀመሩ ተግባራት በኩታ ገጠም እርሻ ገበያ ተኮር ምርቶችን በማምረትና አስፈላጊውን መሰረተ ልማት በማሟላት የአርሶ አደሩን ህይወት የሚቀይሩ ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አንስተዋል። ከግብርናው ባሻገር የገጠር ሽግግርን ለማሳለጥ የተለያዩ ተቋማት ተቀናጅተው የሚሰሩበት የ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። ፍኖተ ካርታው ግብርናውን ማዘመን፣ የገጠር መሰረተ ልማት መሟላት፣ የገበያ ትስስርና እሴት መጨመርን ጨምሮ ወሳኝ ጉዳዮች የተካተቱበት ነው ብለዋል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት በበኩላቸው የግብርና፣ የገጠር እንዲሁም የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ጎን ለጎን ተቀናጅተው እንዲፈጸሙ እየተሰራ ነው ብለዋል። ግብርናን ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር እንደ ሀገር ያሉ ጸጋዎችን መለየትና ገበያ ተኮር ትርፍ ምርት ማምረት ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል። የገጠር ሽግግርን ለማምጣት መሰረት የሚጥሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከእነዚህ መካከል የገጠር ኮሪደር ልማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) የግብርና ትራንስፎርሜሽን የተሻገረ ገጠር ለመፍጠር መሰረት ነው ብለዋል። የግብርና ትራንስፎርሜሽን ትርፍ ምርት ከማምረት ባለፈ፣ ሁሉን አቀፍ መሰረተ ልማት ማሟላትና የነዋሪውን ሕይወት ማሻሻል መሆኑንም ተናግረዋል። የገጠር ትራንስፎርሜሽንን በተሳለጠ መልኩ ለማሳካት የተዘጋጀው ፍኖተ ካርታ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ ያግዛል ብለዋል። የመንግስት፣ የግል እንዲሁም የምርምር ተቋማት ከአጋር ድርጅቶች ጋር መስራት የተሻገረ ገጠር ለመፍጠር ወሳኝ ሚና እንዳለው ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ የሀገሪቱን የፋይናንስ ስርዓት በማሳለጥ የጎላ ሚና አለው
Dec 2, 2025 71
አዲስ አበባ፤ ህዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ የሀገሪቱን የፋይናንስ ስርዓት በማሳለጥ የጎላ ሚና እንዳለው የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚካሄደው ሁለተኛው ቀጣናዊ የካፒታል ገበያ ጉባኤ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄድ ጀምሯል። የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የካፒታል ገበያ የኢትዮጵያን መፃኢ የፋይናንስ ስርዓት የሚያሳልጥ መሰረታዊ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ አካታች የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበች ትገኛለች ብለዋል። ማሻሻያው ወደ ተሟላ ትግበራ ከገባ ወዲህ ማክሮ ኢኮኖሚውን በማረጋጋት ሁሉን አቀፍ ዕድገት ማረጋገጥ በሚያስችል ሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተከትሎ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የሀገር ውስጥ ገቢን በማስፋት ዕምርታዊ ለውጥ መመዝገቡንም ገልጸዋል። በኢኮኖሚ ሪፎርሙ መሰረት ወደ ሥራ የገባው የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን የኢትዮጵያን የፋይናንስ ስርዓት በማሳለጥ ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት። በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ላይ ሪፎርም መደረጉን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ የሚያሳድግ ምቹ የኢንቨስትመንት ምህዳር መፍጠር ተችሏል ብለዋል። ሪፎርሙ ግልጽነትን በመፍጠር፣ በማዕከላዊ ባንክ ላይ ብቻ የተመሰረተውን የፋየናንስ ስርዓት በመቀነስ እና የታክስ መሰረቱን በማስፋት የሚታይ ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል፡፡ የካፒታል ገበያ ሰፊ የስራ ዕድል በመፍጠር ለኢኮኖሚያዊ ሽግግር ወሳኝ መሆኑን አንስተው፤ ለኢትዮጵያ የፋይናንስ ስርዓት ዝማኔ ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ እንደሚያገለግል ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ ተዓማኒና ለግሉ ዘርፍ ተስማሚ የፋይናንስ ምህዳር ለማስፈን በተቋማት መካከል ጠንካራ ትብብር መፍጠር እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡ በአግባቡ የተደራጀ እና የተሟላ መሰረተ ልማት ያለው የካፒታል ገበያ ስርዓት የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለማሳደግና ከዓለም የፋይናንስ ተቋማት ጋር ለማስተሳሰር ያግዛል ብለዋል። የካፒታል ገበያ የኢትዮጵያን መሰረተ ልማት በተለያዩ የቦንድ ኢንቨስትመንት አማካይነት ወደ ሀብት መቀየር የሚያስችል ዕድል መፍጠሩንም ገልጸዋል፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ተቋማት እና ዘርፎች የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀምን የውጤት መለኪያቸው ማድረግ አለባቸው
Dec 2, 2025 125
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ እያንዳንዱ ተቋም እና ዘርፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን አጠቃቀምን የውጤት እና ግብ መለኪያ በማድረግ ሊሰራ እንደሚገባው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። “በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እመርታ” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የማጠቃለያ ስልጠና በሰጡበት ወቅት ካነሷቸው ሀሳቦች መካከል አንዱ የዲጂታል ዘርፉን የተመለከተ ይገኝበታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታል ዘርፉን አስተሳሰሪ አቅም መሆኑን ገልጸው መንግስት የዲጂታል መታወቂያ፣ ሞባይል ባንኪንግ እና ዘመናዊ የክፍያ ዘዴዎች የማስፋት ስራ እያከናወነ መሆኑን አመልክተዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ኳንተም ሳይንስ የሰው ልጆች አኗኗር፣ ስራ እና እሳቤ እየየቀሩ እንደሚገኙም ገልጸዋል። ቴክኖሎጂን መቀበል አለብን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የኃይልን፣ የምርት እና የተሳትፎ ሕግጋትን እንደገና እየጻፈ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ፋይዳ፣ ፓስፖርት፣ መሶብ፣ ሞባይል ባንኪንግ፣ ዘመናዊ የክፍያ ዘዴ፣ የጉምሩክ እና ገቢዎች ዲጂታል አገልግሎት እንዲሁም የተቀናጀ የፋይናንስ አስተዳደር መረጃ ሥርዓት(ኢፍሚስ) በሀገር ውስጥ አቅም እየጎለበተ እና እያደገ መሄድ እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የተለያዩ ዘርፎች ምን ያህል ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ተጠቅመዋል? ብለን ከአሁኑ መለካት ካልጀመርን ዘመን መዋጀትን ብንፈልግም አንደርስበትም ነው ያሉት። ለሁሉም ስራ ቴክኖሎጂን መጠቀም እንደሚያስፈልግ ጠቁመው የተሟላ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ጋር ማስተሳሰር ግድ እንደሚል አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአንድ ግቦች በሚል ባነሱት ሀሳብ እያንዳንዱ ከተማ የአንድ መሶብ አገልግሎት መክፈት እንዳለበትም አንስተዋል። በ100 ፐርሰንት ግቦች ውስጥም የፋይዳ መታወቂያ ሙሉ ለመሉ በኢትዮጵያ መዳረስ እንዳለበት ገልጸው ለዚህም በሁሉም የአስተዳደር መዋቅሮች አበክሮ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ በጣም ወሳኝ ስራ መሆኑን ጠቁመውም ኢኒሼቲቩ መቶ ፐርሰን መሳካት አለበት ብለዋል። እያንዳንዱ ተቋም እና ዘርፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ምን ያህል ተጠቀምኩኝ? በሚል ግብ ማስቀመጥ እንደሚኖርበትም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት። የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ካላደገ የሚታሰበውን ትራንስፎርሜሽንና ትስስር ማምጣት እንደማይቻልም አመልክተዋል። በፈጠራ እና ፍጥነት ጥራትንና ብዛትን እውን ለማድረግ መትጋት የመደመር መንግስት ቁልፍ ስራ ነው ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት መሰረት የሆኑ ቁልፍ ስኬቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል
Dec 1, 2025 204
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት መሰረት የሆኑ ቁልፍ ስኬቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉቀን ቀሬ ገለጹ። የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተተከሉ ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎችን በይፋ አገልግሎት አስጀምሯል። የContinious Operating Reference Station /CORS/ -ጣቢያ በቋሚነት መሬት ላይ የሚተከል የሳተላይት መረጃን ያለማቋረጥ የሚቀበልና የሚያደራጅ ቴክኖሎጂ ነው ተብሏል። እንዲሁም የአንድን ቦታ መገኛ ከጂ ፒ ኤስ ሳተላይቶች 24 ሰዓት በመቀበል ከፍተኛ ጥራት ያለው መረጃ የሚያቀርብ እንደሆነም ተገልጿል። የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉቀን ቀሬ እንደገለጹት፥ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ባለፉት አምስት ዓመታት ለዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት መሰረት የሆኑ ቁልፍ ስኬቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል። የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በማስጀመረ፣ በቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ግንባታ፣ በህግ ማእቀፎች እንዲሁም በ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ በክህሎት ግንባታ ለውጥ መምጣቱን ጠቁመዋል። ከሳተላይት መረጃ መቀበያ ጀምሮ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ሠፋፊ ተግባራት መከናወናቸውን በማንሳት፥ በቀጣይም ለዲጅታል መሠረተ ልማትና ለዲጅታል ኢኮኖሚ መስፋፋት በትብብር እንደሚሠራ ጠቁመዋል። የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን በበኩላቸው፥ ዛሬ ሥራ የጀመሩት ጣቢያዎች በከተሞች እየተመዘገበ ያለውን እመርታዊ ለውጥ በማጠናከር ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አንስተዋል። በተለይም ከተሞችን በፕላን እንዲሁም በከተሞች ያለ መሬትን ቆጥሮ መዝግቦ በፍትሀዊነት ለመምራት እና የቅየሳን ትክክለኛነትን ለማረጋገጥ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖራቸው ጠቅሰዋል። ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በቀጣይም 14 ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎች (Continious Operating Reference Station /CORS/ ለመገንባት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ (ዶ/ር)፥ ዛሬ ሥራ የጀመሩት መረጃ ተቀባይ ጣቢያዎች ለቅየሳ ሙያተኞች፣ ለተመራማሪዎች፣ ለአደጋ ስጋት ተንታኞች፣ ለመልክዓ ምድር እና ለልዩ አገልግሎት ካርታ አዘጋጅ ባለሙያዎች የቦታዎችን አሁናዊ ሁኔታ መረጃ ለማግኘት እንደሚያስችሉ ገልጸዋል። የህንጻ፣ የመንገድ፣ የድልድይ እና ግድብ ግንባታ ፕሮጀክቶች ጥራት ባለው ጂኦስፓሻል መረጃ ላይ ተመስርተው እንዲነደፉና እንዲገነቡ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው ጠቁመዋል። የግብርና፣ የኢንዱስትሪ፣ የማዕድንና ሌሎች የኢኮኖሚ ዘርፎች እንዲዘምኑ በቂ መረጃ በማቅረብ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖራቸውም ነው ያነሱት። በተጨማሪም የመሬት አስተዳደር ዘመናዊ እና ጥራት ያለው እንዲሆን ያስችላሉ ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ ጣቢያዎቹን ለቅየሳ ስራዎች እና ለካርታ ዝግጅት እንዲሁም ምርምር ለመስራት በሰፊው እንደሚጠቀምባቸው አንስተዋል።
የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎችን አገልግሎት አስጀመረ
Dec 1, 2025 225
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተተከሉ ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎችን በይፋ አገልግሎት አስጀምሯል። የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን በዚሁ ወቅት፥ ዛሬ ሥራ የጀመሩት ጣቢያዎች በከተሞች እየተመዘገበ ያለውን እመርታዊ ለውጥ በማጠናከር ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አንስተዋል። በተለይም ከተሞችን በፕላን እንዲሁም በከተሞች ያለ መሬትን ቆጥሮ መዝግቦ በፍትሀዊነት ለመምራት እና የቅየሳን ትክክለኛነትን ለማረጋገጥ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖራቸው ጠቁመዋል። በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ አሰጣጥን በማዳበር እና ተጠቃሚዎች በቀላሉ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላሉ ነው ያሉት። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በቀጣይም 14 ከሳተላይት ያለማቋረጥ መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎች (Continious Operating Reference Station /CORS/ ለመገንባት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉቀን ቀሬ በበኩላቸው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለዲጂታል ልማት መሰረት የሆኑ ቁልፍ ስኬቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን ጠቁመዋል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ሠፋፊ ተግባራት መከናወናቸውን በማንሳት፥ በቀጣይም ሚኒስቴሩ ከሳተላይት መረጃ የሚቀበሉ ጣቢያዎችን ለማስፋፋት በትብብር እንደሚሠራ ጠቁመዋል። የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ (ዶ/ር)፥ ዛሬ ሥራ የጀመሩት መረጃ ተቀባይ ጣቢያዎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተሟላላቸው ናቸው ብለዋል። ለቅየሳ ሙያተኞች፣ ለተመራማሪዎች፣ ለአደጋ ስጋት ተንታኞች፣ ለመልክዓ ምድር እና ለልዩ አገልግሎት ካርታ አዘጋጅ ባለሙያዎች የቦታዎችን አሁናዊ ሁኔታ መረጃ ለማግኘት እንደሚያስችሉ ገልጸዋል። የህንጻ፣ የመንገድ፣ የድልድይ እና ግድብ ግንባታ ፕሮጀክቶች ጥራት ባለው ጂኦስፓሻል መረጃ ላይ ተመስርተው እንዲነደፉና እንዲገነቡ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው ጠቁመዋል። የግብርና፣ የኢንዱስትሪ፣ የማዕድንና ሌሎች የኢኮኖሚ ዘርፎች እንዲዘምኑ በቂ መረጃ በማቅረብ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖራቸውም ነው ያነሱት። በተጨማሪም የመሬት አስተዳደርን ዘመናዊ እና ጥራት ያለው እንዲሆን ያስችላሉ ብለዋል። ኢንስቲቲዩቱ ይህን ጣቢያዎቹን ለቅየሳ ስራዎች እና ለካርታ ዝግጅት እንዲሁም ምርምር ለመስራት በሰፊው እንደሚጠቀምባቸው አንስተዋል። የContinious Operating Reference Station /CORS/ -ጣቢያ በቋሚነት መሬት ላይ የሚተከል የሳተላይት መረጃን ያለማቋረጥ የሚቀበልና የሚያደራጅ ቴክኖሎጂ ነው ተብሏል። እንዲሁም የአንድን ቦታ መገኛ ከጂ ፒ ኤስ ሳተላይቶች 24 ሰዓት በመቀበል ከፍተኛ ጥራት ያለው መረጃ የሚያቀርብ እንደሆነም ተገልጿል።
የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው የዲጂታል ግብርና ኮንፍረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ይጀመራል
Dec 1, 2025 185
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው የዲጂታል ግብርና ኮንፍረንስ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል። “ኢኖቬሽን እና የዲጂታል መፍትሄዎችን ጠንካራ፣ አረንጓዴ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብርና ዘርፍ ግንባታ በመጠቀም የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ ብሩህ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የዲጂታል ግብርና ኤክስቴሽን አገልግሎት፣ የግብርና ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን፣ የገበያ ተደራሽነት፣ የእሴት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የግብርና ምርታማነትን ከአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም መገንባት ጋር ያስተሳሰረ አካሄድን መከተል፣ የግብርና ፖሊሲዎችና የህግ ማዕቀፎች ትግበራ በኮንፍረንሱ የሚመከሩባቸው አጀንዳዎች ናቸው። ኮንፍረንሱ የእውቀት ሽግግር እና ፖሊሲ ተኮር ውይይቶች የሚደረግበት ሲሆን ስኬታማ የሀገራት የግብርና ኢኒሼቲቮች ለተሳታፊዎች ይቀርቡበታል። በአፍሪካ የዲጂታል ግብርና መፍትሄዎችን ተደራሽነት የሚደግፉ ስትራቴጂዎች የመለየት እና አጋርነቶችን ማጠናከር ከሁነቱ የሚጠበቅ አበይት ውጤት መሆኑን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ 2024 ያፀደቀውን አህጉራዊ የዲጂታል ግብርና ስትራቴጂ ተፈጻሚነት የማሳደግ ጥረት አካል መሆኑንም አመልክቷል። የግብርና ስትራቴጂው ከአጀንዳ 2063 እና ከረጅም ጊዜ የአፍሪካ የልማት እቅድ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ነው ህብረቱ የገለጸው። ስትራቴጂው ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ(አይሲቲ) በመጠቀም አህጉራዊ የዲጂታል ገበያ መገንባት እና ግብርናን ከአፍሪካ የዲጂታልና ዘላቂ ልማት ግቦች ጋር የማስተሳሰር ግብ ያለው ነው። እስከ ሕዳር 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው በዚህ መድረክ የአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ፖሊሲ አውጪዎች፣ የግብርና ተመራማሪዎች እና ሳይንቲስቶች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች፣ አርሶ አደሮች እና የአርሶ አደር ተቋማት፣ የምርምር ተቋማት፣ባለሀብቶች፣ የልማት አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ።
ስፖርት
በተጠባቂው ጨዋታ ባርሴሎና አትሌቲኮ ማድሪድን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ
Dec 3, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ በስፔን ላሊጋ ሳምንት የ15ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ባርሴሎና አትሌቲኮ ማድሪድን 3 ለ 1 አሸንፏል። ማምሻውን በካምፕ ኑ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ራፊኒያ፣ ዳኒ ኦልሞ እና ፌራን ቶሬስ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። አሌክስ ባኤና ለአትሌቲኮ ማድሪድ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። በጨዋታው ላይ ባርሴሎና ያገኘውን ፍጹም ቅጣት ምት ሮበርት ሌዋንዶስኪ ሳይጠቀምበት ቀርቷል። በሊጉ 12ኛ ድሉን ያስመዘገበው ባርሴሎና በ37 ነጥብ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል። ከተከታዩ ሪያል ማድሪድ ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ከፍ አድርጓል። በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አትሌቲኮ ማድሪድ በ31 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። በ33 ነጥብ በሊጉ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሪያል ማድሪድ ነገ ከሜዳው ውጪ ከአትሌቲኮ ቢልባኦ ጋር ያደርጋል።
ዘጠኝ ግቦች በተቆጠሩበት አዝናኝ ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን አሸነፈ
Dec 3, 2025 47
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 5 ለ 4 አሸንፏል። ማምሻውን በክራቫን ኮቴጅ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፊል ፎደን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር አርሊንግ ሃላንድ፣ ታጃኒ ራይንደርስ እና የፉልሃሙ ሳንደር በርገ በራሱ ላይ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ሳሙኤል ቹኩዌዜ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ኤሚል ስሚዝ ሮው እና አሌክስ ኢዎቢ ቀሪዎቹን ግቦች ለፉልሃም አስቆጥረዋል። ማንችስተር ሲቲ 5 ለ 1 እየመራ ሶስት ግቦችን ማስተናገዱ በጨዋታው ማብቂያ ላይ ውጥረት ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል። በሊጉ ዘጠነኛ ድሉን ያስመዘገበው ማንችስተር ሲቲ በ28 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ፉልሃም በ17 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ 100ኛ ግቡን አስቆጥሯል። ሃላንድ በሊጉ ፈጣን 100 ግብ አስቆጣሪ በመሆን አዲስ ታሪክ ሰርቷል። ተጫዋቹ ግቦቹን ከመረብ ላይ በማሳረፍ 111 ጨዋታዎች ወስዶበታል። ከዚህ ቀደም አለን ሺረር በ124 ጨዋታዎች 100 ግቦችን በማስቆጠር ለ30 ዓመታት ክብረ ወሰኑን ይዞ ቆይቷል። በሌሎች መርሃ ግብሮች ኤቨርተን በጃክ ግሪሊሽ ጎል ቦርንማውዝን ከሜዳው ውጪ 1 ለ 0 አሸንፏል። ኒውካስትል ዩናይትድ እና ቶተንሃም ሆትስፐርስ ያደረጉት ጨዋታ ሁለት አቻ ተጠናቋል። ብሩኖ ጉማራይሽ በጨዋታ እና አንቶኒ ጎርደን በፍጹም ቅጣት ምት ለኒውካስትል ግቦቹን አስቆጥረዋል ። ክርስቲያን ሮሜሮ ለቶተንሃም ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፏል።
ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድኑ የ10 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበረከተ
Dec 2, 2025 126
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ):- የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ለአፍሪካ ዋንጫ ላለፈው ለኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን የ10 ሚሊዮን ብር የገንዝብ ሽልማት አበርክቷል። ሚኒስቴሩ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድኑ ማምሻውን የእራት ግብዣ አድርጓል። ሚኒስቴሩ በመርሐ ግብሩ ላይ የ10 ሚሊዮን ብር ሽልማት ለብሄራዊ ቡድኑ ያበረከተ ሲሆን የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ የገንዘብ ሽልማቱን አስረክበዋል። ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በወቅቱ የተገኘው ስኬት የመንግስትና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የጋራ ስራ ውጤት እንደሆነ ተናግረዋል። ብሄራዊ ቡድኑ በአፍሪካ ዋንጫው ተሳትፎው ውጤታማ ጊዜ እንዲያሳልፍ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል። በመርሐ ግብሩ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጅራ እና ሌሎች የፌዴሬሽኑ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ማጣሪያ ዛሬ ከኬንያ አቻው ጋር ባደረገው የደረጃ ጨዋታ 3 ለ 0 በማሸነፍ ለአህጉራዊው መድረክ ማለፉን አረጋግጧል። ብሄራዊ ቡድኑ ከ22 ዓመታት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ይመለሳል። ኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ውድድር ላይ ስትሳተፍ የሞሮኮው ለአራተኛ ጊዜ ነው።
በፕሪሚየር ሊጉ ነጌሌ አርሲ እና ሸገር ከተማ አቻ ተለያዩ
Dec 2, 2025 69
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የስምንተኛ ሳምንት መርሐግብር ነጌሌ አርሲ እና ሸገር ከተማ ያደረጉት ጨዋታ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ማምሻውን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጀቤሳ ሚኤሳ በ55ኛው እና በ70ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ሸገር ከተማ መሪ ሆኖ ነበር። ይሁንና ከቤ ብዙነህ በ75ኛው እና ሮሆቦት ሰላሎ በ93ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፏቸው ጎሎች ነጌሌ አርሲን አቻ አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ ነጌሌ አርሲ በ10 ነጥብ ደረጃውን ከ12ኛ ወደ 11ኛ ከፍ አድርጓል። አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ሸገር ከተማ በዘጠኝ ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታውን ተከትሎ የስምንተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የዘጠነኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከሕዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ይካሄዳሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በኢሉባቦር ዞን በክረምቱ ወቅት የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ እየተከናወነ ነው
Dec 2, 2025 104
መቱ ፤ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፡-በኢሉባቦር ዞን በክረምቱ አረንጓዴ አሻራ መርሐግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በዘመቻ መልክ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የዞኑ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ሰራተኞች የተሳተፉበት በክረምቱ ወቅት የተተከሉ ችግኞችን በጋራ እየተንከባከቡ ናቸው። የኢሉባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አወል መሐመድ በዞኑ በክረምቱ ወራት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰዋል። የችግኞቹን የጽድቀት መጠን ለማሳደግም ህብረተሰቡ እንክብካቤ እንዲያደርግ ግንዛቤ በመፈጠሩ የዞኑ የመንግስት ሰራኞችን ጨምሮ ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍሎች ባሳተፈ መልኩ እንክብካቤው በዘመቻ መልክ እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም የጽድቀት መጠናቸው በአሁኑ ወቅት ከ95 በመቶ በላይ መድረሱን ተናግረዋል። ለችግኞቹ የሚደረገው እንክብካቤ ጽድቀታቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ በአጭር ግዜ ደርሰው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው እንዲጎላ እንደሚያግዝም አመልክተዋል። በችግኝ እንክብካቤው ከተሳተፉ የመንግስት ሰራተኞች መካከል የዞኑ የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽሕፈት ቤት ባለሞያ አቶ መላኩ ከበደ በበኩላቸው በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአንድነት የተከልናቸውን ችግኞች በአንድነት የመንከባከብ ስራ እየሰራን ነው ብለዋል። በመንግስት አገልግሎት ለህዝብ ከሚሰጧቸው አገልግሎት ባለፈ በክረምቱ ወራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከሏቸውን ችግኞች በመንከባከብ እንዲጸድቁ ለማድረግ በስፍራው መገኘታቸውን ገልጸዋል። በአረንጓዴ አሻራ የተከልሏቸው ችግኞች የሚጠበቀውን ውጤት ለማግኘት መትከል ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የእንክብካቤ ስራውን ማጠናከር በማስፈለጉ ለዚሁ ተግባር መጥቻለሁ ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ፋጡማ የሱፍ ናቸው። አቶ እንዳሻው ጆቴ በበኩላቸው የተተከሉ ችግኞችን በጋራ በመንከባከብ ለውጤት ለማብቃት ያልተቋረጠ ክትትል በማስፈለጉ በተከላ ወቅቱ የገቡትን ቃል በተግባር ለማዋል ስራው ላይ መገኘታቸውን ጠቁመዋል። በክረምቱ የተተከሉት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተገቢው እንክብካቤ ካልተደረገላቸው በመጥፋት የወጣባቸው ከፍተኛ ገንዘብ ለብክነት እንደሚዳረግም አክለዋል።
ኢትዮጵያውያን የደመቁበት የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ
Dec 1, 2025 171
ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ ተከናውኗል። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ የሽልማት መርሃ ግብሩ የሚዲያ አጋር ሲሆን የሁለት ቀኑን የሽልማት መርሃ ግብር የቀጥታ ስርጭት ሽፋን በመስጠት ለመላው አፍሪካውያን ተደራሽ አድርጓል። የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ(አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ አድርጓል። የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያን ጎብኝተዋል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች ተከናውኗል። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ያስገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ከ94ቱ ኢትዮጵያውያን የሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ሶስቱ በተለያዩ ዘርፎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የ2025 የሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ አሸናፊ በመሆን ሽልማቱን ተቀብሏል። ጋዜጠኛ ጌትነት ሸንቁጤ ሽልማቱን የተጎናጸፈው “Climate Intelligence for Survival: IGAD’s Push for Accurate, Actionable Data” በሚል ርዕስ በጻፈው ጽሁፍ ነው። የጋዜጠኛ ጌትነት ጽሁፍ በኢጋድ ቀጣና ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና የሚዳስስ ነው። በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰት ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋዎችና ኢ-ተገማች የአየር ጸባይ ለውጦች ዜጎችን በማፈናቀል እና በቁም እንስሳት ላይ ያደረሱትን ጉዳት ይቃኛል። ትክክለኛ፣ ጊዜውን የጠበቀና ለተግባር ምላሽ የሚያገለግሉ የአየር ንብረት መረጃዎች የማይበገር አቅም ለመገንባትና አደጋዎችን ለመከላከል ያላቸውን ሚናም ተዳሷል። በጽሁፉ ላይ የኢጋድ የአየር ንብረት ትንበያና ትግበራ ማዕከል(ICPAC) የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን በማጠናከር፣ የትንበያ አቅም ማሳደግና የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት የመቋቋም አቅም ላይ እያከናወነ ያለው ስራ ተቀምጧል። የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች፣ የአንበጣ መንጋ፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብና ሌሎች ፈተናዎችን ለመከላከል ተአማኒነት ያለው የአየር ንብረት መረጃ ወሳኝ መሆኑም ተመላክቷል። በተለይም ኑሯቸው በተለያዩ ወቅቶች ላይ ለተመረኮዙ አርሶ እና አርብቶ አደሮች መረጃው ወሳኝ መሆኑን ያስቀምጣል። ሌላኛው ተሸላሚ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (ኦቢኤ) ጋዜጠኛ ሽመክት ጉግሳ ነው። የተሸለመበት ዘርፍ በኦሮምኛ ቋንቋ በሰራው ፕሮግራም ነው። ፕሮግራሙ ዛፎች ከሰው ህይወት ጋር ያላቸውን ቁርኝት በዋናነት ይቃኛል። መንደርደሪያውን ከዓለም የዛፍ ጠቀሜታና ጥበቃ በማድረግ በኦሮሚያ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ይዳስሳል። ዛፍ መትከል ተፈጥሮና የሰው ልጅን እንዴት እንደሚጠብቅ በተቃራኒው መቁረጥ የሚያደርሰውን ጉዳትም ያስቃኛል። የ21 ደቂቃ ፕሮግራሙ የኦሮሞ ህዝብ በዘመናት መካከል ዛፎችና የደን ሀብቶች እንዲጠበቁ ያደረገው አስተዋጽኦ ተወስቶበታል። በተለይም በገዳ ስርዓት ውስጥ ዛፍን መጠበቅ ያለው ሚና በስፋት ተነስቷል። አንድ ዛፍ ለአራት ሰዎች መኖር መሠረት ይሆናል፤ ዛፍ መቁረጥ አራት ሰዎችን እንዲሞቱ ያደርጋል የሚል የአባገዳ አስተያየትም ተጠቃሽ ነው። አባ ገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ እናቶችና የአካባቢ ማህበረሰቦች ተፈጥሮን ጠብቆ በማቆየት ያላቸው ሚና ቁልፍ እንደሆነ ተመላክቷል። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መስራችና ስራ አስኪያጅ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን(ኢጋድ) የህይወት ዘመን ጋዜጠኝነት ሽልማት ተበርክቶላታል። ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በሬዲዮ ጋዜጠኝነት ግንባር ቀደምና በዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቷንም ኢጋድ ገልጿል። በብሮድካስት ሚዲያው ከ40 ዓመት በላይ የቆየችው ጋዜጠኛ መዓዛ ሸገር ኤፍኤም 102.1ን ከ18 ዓመታት በፊት በማቋቋም በኢትዮጵያ ቀዳሚ የመረጃ እና የመዝናኛ ጣቢያ እንዲሆን ማድረጓ አመልክቷል። ከጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ አበይት ፕሮግራሞች መካከል “ማንን ምን እንጠይቅልዎ?” እና “ሸገር ካፌ” ተጠቃሽ ናቸው። ጋዜጠኛዋ በፕሮግራሞቹ ህዝብን ከመንግስት አገልግሎቶች ጋር በማገናኘትና በማህበራዊ፣ የህግ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ላይ የተመረኮዙ ውይይቶች እንዲካሄዱ መድረክ መፍጠር መቻሏንም ነው የገለጸው። የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መሪ ሀሳብ በሆነው የእናንተ ሬዲዮ መዓዛ በጋዜጠኝነት ሙያ ህዝብን ለማገልገልና የኢትዮጵያውያንን ድምጽ ለማጉላት ያላትን ቁርጠኝነት ኢጋድ አድንቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ኢጋድ አመልክቷል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Dec 1, 2025 153
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በሚቀጥሉት አስር ቀናት ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንደገለፀው በሚቀጥሉት አሥር ቀናት ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት አካባቢዎች ላይ ቀጣይነት ይኖረዋል። ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጥቂት የደቡብ እና የደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናቶች ላይ በተዳከመ ሁኔታ ቀጣይነት ይኖራቸዋል። በዚህም የደቡብ ኦሮሚያ ዞኖች፤ የሲዳማ ክልል ዞኖች፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡባዊ ዞኖች እና የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ዞኖች በጥቂት ስፍራዎቻቸው ላይ በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚጠቁሙ ገልጿል። በሌላ በኩል ከሚኖረው የደመና ሽፋን ላይ በመነሳት በጥቂት የሰሜን፣ መካከለኛውና ደቡብ ጎንደር ዞኖች፣ ባህርዳር ዙሪያ፣ አዊ ፣ በምዕራብና ምስራቅ ጎጃም አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናት ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ትንበያው አብራርቷል። የምዕራብ ኦሮሚያ ክልል ዞኖች፣ አርሲ እና ምዕራብ አርሲ፤ ባሌ እና ምስራቅ ባሌ ዞኖች፣ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ እና የማኦኮሞ ልዩ ዞን፤ የጋምቤላ ክልል ዞኖች፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዞኖችም አልፎ አልፎ ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ። ስለሆነም በሚኖሩት ደረቅ ቀናቶች የደረሱ ሰብሎች መሰብሰብ አስፈላጊ መሆኑን ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል። በሌላ በኩል ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ሀገሪቱ የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩም በመግለጫው ተብራርቷል። በዚህም የበጋው ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በተለይም በሰሜን፣ ምስራቅ፣ መካከለኛውና ደቡብ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የለሊትና የማለዳው ቅዝቃዜ ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየስ በታች እንደሚሆን ትንበያው ያሳያል።
የኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤን ለማስተናገድ መመረጥ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ላላት ቁርጠኝነት የተሰጠ ዕውቅና ነው
Nov 30, 2025 168
አዲስ አበባ፤ ህዳር 21/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤን ለማስተናገድ መመረጥ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ላላት ቁርጠኝነት የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል በሚደረግ ሂደት የሚዲያ ሚና ወሳኝ መሆኑንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ''ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ፤ ደኅንነቱ ለተረጋገጠ ጠንካራና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሃሳብ የ2025 የሚዲያ ሽልማት በአዲስ አበባ በማካሄድ ላይ ይገኛል። በመድረኩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ኢጋድ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለቀጣናዊ የአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስም በስትራቴጂክ ዕቅድ መምራት የሚያስችል የማስተባበር ሥራ እየሰራ አንደሚገኝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ በተግባር የተደገፈ ለውጥ አምጪ የመፍትሔ እርምጃዎች ላይ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ለጎረቤት ሀገራት ጭምር በማጋራት ውጤታማ ስራ ማከናወኗን አስረድተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአህጉሪቷ የታዳሽ ኃይል መስክ አዲስ ምዕራፍ በመክፈት የዲጂታል ሽግግር አንቀሳቃሽ ኃይል ለመሆን መብቃቱን አንስተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና ሌሎች የታዳሽ ሀይል የልማት ስኬቶች ለአፍሪካ የኢንዱስትሪና የዲጂታል ሽግግር በምሳሌነት የሚወሰዱ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የኢኮኖሚ ግንባታም 2ኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በስኬት በማስተናገድ ቀርጠኝነቷን ለዓለም ማስመስከሯን ገልጸዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላ የሚካሄደውን የመንግስታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP 32) በ2027 ለማስተናገድ በሙሉ ድምጽ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ ላላት ቁርጠኝነት የተሰጠ እውቅና መሆኑን ተናግረዋል። የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመዋጋትም መገናኛ ብዙኃን ግንባር ቀደም ሚና እንዳላቸው የኢጋድ 2025 የጋዜጠኞች ዕውቅና ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ እያደገ የመጣው የመገናኛ ብዙኃን ሙያተኞች ሽልማት ቀጣናዊ ድምፆችን ለማጉላት ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። መገናኛ ብዙኃን ሙያተኞችም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ሰላምና ደኅንነትን ለማስጠበቅ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም የቀጣናውን ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሻሽል ወሳኝ የልማት እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። በብራዚል ቤለም በተካሄደው 30ኛ ጉባኤ ላይ ከሁለት ዓመታት በኋላ የሚካሄደውን 32ኛ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ (COP-32) ኢትዮጵያ እንድታስተናግድ መመረጧ ይታወቃል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 153
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 551
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 443
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል። ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል። ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ለሱዳን ግጭት ዓለም አቀፍ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል- ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)
Nov 19, 2025 554
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ የሱዳን ግጭት ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቀናጀ ምላሽ እንዲሰጥ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ያዘጋጀው ሁለተኛ የሱዳን የልዩ ልዑኮች ፎረም ዛሬ በጅቡቲ ተካሄዷል። በፎረሙ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ተዋንያን ተሳትፈዋል። ፎረሙ በሱዳን ላለው ቀውስ የተቀናጀ መልስ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በፎረሙ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር የሱዳን ሰላም በሱዳናውያን የሚመራ፣ ቀጣናዊ ትብብር የተረጋገጠበት እና ዓለም በአንድ ድምጽ የሚደግፈው ሊሆን እንደሚገባ አመልክተዋል። በሱዳን ያለውን ግጭት ለማስቆም፣ ንጹሃን ዜጎችን ለመጠበቅ እና የኢጋድ ቀጣናን የተረጋጋ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ዋና ፀሐፊው ኢጋድ ከአፍሪካ ህብረት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን በሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደረስ፣ የሰብዓዊ እርዳታ መተላለፊያ እንዲከፈት እና ተአማኒነት ያለው የስልጣን ሽግግር እንዲኖር በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። ኢጋድ ሱዳናውያን በሀገራቸው ሰላም እና ደህንነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ክብራቸው እንዲጠበቅ ያላቸው መሻት እንዲሳካ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በመረጃው አመልክቷል።
ሐተታዎች
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 295
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል። የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 616
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 644
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው። በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው። የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው። “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል። በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 696
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2605
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2641
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3537
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3622
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 1860
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1229
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7046
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5537
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ብልህ ከችግር ይማራል!!
Dec 2, 2025 118
ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል!! በማሙሽ ጋረደው ገራድ ተስፋዬ ተፈራ ትውልድና እድገታቸው በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ቃልሻ ቀበሌ ሲሆን በ1999 ዓ.ም በህገ ወጥ መንገድ ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው እንደነበር ያስታውሳሉ። ገንዘብ ለማግኘትና የመለውጥ ህልማቸውን ለማሳካት በሚል ሩቅ አስበው የጀመሩት ህገ ወጥ ጉዞ መዳረሻውን እስር ቤት አደረገው። ይህም ሁኔታ ''ሩቅ አሳቢ-ቅርብ አዳሪ'' አደረጋቸው። በባዕድ አገር በነበራቸው የ2 ዓመት የእስር ቤት ቆይታም የምግብ እጦትን ጨምሮ አካላዊ ጥቃትና ጉልበት ብዝበዛ እንዲሁም የተለያዩ ስነ-ልቦናዊ ጉዳቶችን እንዳስተናገዱ ይናገራሉ። ይህም አልበቃ ብሎ ከአካባቢው በህገወጥ መንገድ የሚሰደዱ ወጣቶችን ጉልበት በመጠቀም ሰፋፊ እርሻዎች ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ የጉልበት ብዝበዛ ይፈፀምባቸው እንደነበርም ያስታውሳሉ። ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል! የሚሉት ገራድ ተስፋዬ ሩቅ ሳይጓዙ፣ ገንዘብ ሳያወጡ ሰርተው መለወጥ የሚችሉበትን አካባቢያቸውን ፀጋ ሳያማትሩ ስደት መሄዳቸው ቁጭት ፈጥሮባቸው ነበር፡፡ ይህም በሀገራቸው እንኳንስ የለማን መሬት ይቅርና የተቦረቦረ መሬትን አልምቶ ጉልበትንና ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ለስኬት መብቃት እንደሚቻል ከእስር ቤት ቆይታቸው ተምረው ከእስር እንደተፈቱም ወዲያውኑ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን ተናግረዋል። በ2001 ዓ.ም ወደ ሀገር ቤት እንደተመለሱም በማህበር ተደራጅተው ከመንግሥት ባገኙት 70 ሺህ ብር ብድር በእንስሳት እርባታ ላይ ለመሰማራት 4 የወተት ከብቶችን ገዝተው የእርባታ ስራ መጀመራቸውን ይገልጻሉ፡፡ በዚህም የዞኑ አስተዳደር የሰጣቸውን መሬት አልምተው የእንስሳት እርባታውን አስፋፍተው መስራት ጀመሩ፡፡ አሁን ላይ የወተት ላሞቹን ቁጥር 37 በማድረስ የወተት ምርታማነታቸው አድጎ ከቤት ፍጆታ አልፎ ለሆሳዕና ከተማና አካባቢው በቀን ከ670 ሊትር በላይ ወተት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ለ40 ወጣቶችም ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ከመፍጠራቸውም ባሻገር የተለያዩ የጭነትና የስራ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራት መቻላቸውን ይናገራሉ። የጀመሩትን ስራ በጥምር ግብርና የማስፋትና የሚያገኙትን ወተት በማቀነባበር ምርቱን በተለያየ መልኩ ለገበያ የማቅረብ ራዕይን ሰንቀው በትጋት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በህገወጥ ስደት ካጋጠማቸው ችግር ተነስተው በተግባር ያዩትን ለሌሎች በማስተማር የስደትን አስከፊነት ለአካባቢያቸው ወጣቶች እያስገነዘቡ መሆኑን ገልጸዋል። ወጣቶች የስደትን አማራጭ ከመመልከታቸው በፊት የአካባቢያቸውን ፀጋ እንዲቃኙና ራዕይ ሰንቀው ራሳቸውን ለማሻሻል እንዲሰሩም መክረዋል። መለወጥ በውጪ ሀገር ብቻ ያለ የሚመስላቸው የቤተሰብ ኃላፊዎችም ልጆቻቸው በሀገራቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ በማመን ሊያግዟቸው እንደሚገባም አቶ ገራድ አስገንዝበዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደስላሴ፤ በክልሉ በርካታ ወጣቶች ያልተጨበጠ ተስፋ ሰንቀው ለህገወጥ ስደትና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ የሚያስችል አቅም በግብርናው ዘርፍ መኖሩን ጠቅሰው በዘርፉ የተሰማሩ ከስደት ተመላሾች በአካባቢያቸው ሰርተው ለስኬት እየበቁ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ ስራ አጥ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ላይ የሚገኙና የእነዚህን አካላት ተሞክሮ በመውሰድ በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡
ዲጂታል ግብርና፤ የአፍሪካ ግብርና አዲስ ምዕራፍ
Dec 1, 2025 167
ዲጂታል ግብርና በጥቅሉ ሲተረጎም የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ለግብርና ስራዎች መጠቀም ማለት ነው። ቴክኖሎጂዎቹ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የገበያ ተደራሽነትን በማስፋት፣ በአቅርቦት የእሴት ሰንሰለት ላይ መጠናከር፣ በቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓት፣ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀምና የአየር ንብረት ለውጥ አይገበገሬነት ስራዎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አላቸው። የዓለም የዲጂታል ግብርና ገበያ እ.አ.አ በ2022 ከ10 እስከ 12 ቢሊዮን መድረሱን የተለያዩ መረጃዎች ያመለክታሉ። እ.አ.አ በ2028 የገበያ መጠኑ ከ23 እስከ 25 ቢሊየን ዶላር እንደሚደርስ ትንበያ ተቀምጧል። የዲጂታል ግብርና በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ እና እስያ ፓሲፊክ በፍጥነት እያደገ ሲሆን በአፍሪካና ላቲን አሜሪካ ጅምር ላይ ነው ማለት ይቻላል። ሰሜን አሜሪካ 40 በመቶ እና አውሮፓ 25 በመቶ የዓለም የዲጂታል ግብርና ገበያ ድርሻን ይይዛሉ። አርሶ አደሮች ለዲጂታል ግብርና የሚያስፈልጋቸውን ቴክኖሎጂዎችን አለማግኘት፣ የዳታ ደህንነት እና የግል መረጃ ጥበቃ፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የኢንተርኔት ተደራሽነትና ባህላዊ ልማዶችን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር ማስተሳሰር ዓለም አቀፍ የዘርፉ ፈተናዎች ናቸው። አፍሪካ ከአምስት እስከ ሰባት በመቶ(ከ500 እስከ 800 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር) የሚገመት ነው። በአፍሪካ የግብርና ቴክኖሎጂ ያለው ኢንቨስትመንት በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ዘርፉ ከ400 ሚሊየን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ፈሶበታል። በሞባይል የማማከር አገልግሎት፣ የገበያ ትስስር ማዕቀፎችና ለአርሶ አደሮች የፋይናንስ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የቴክኖሎጂዎቹ የተደራሽነትና አላምዶ የመጠቀም ውስንነት፣ የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የፖሊሲ እና የህግ ማዕቀፍ እክሎች እንዲሁ አካታችነት የአፍሪካ ፈተናዎች ናቸው። በአፍሪካ አብዛኛው ግብርና በአነስተኛ ይዞታ ባላቸው አርሶ አደሮች ላይ የተመሰረተ ሲሆን ግብርና ለአፍሪካውያን ኑሮ እና የምግብ ዋስትና ወሳኝ የሚባል ነው። በዚህ ረገድም የዲጂታል ግብርና ለግብርና ምርታማነት ማደግ፣ የአቅርቦት እጥረትን በመቅረፍና የልማት ግቦች በማሳካት ረገድ የበኩሉን ሚና ይጫወታል። ኢትዮጵያ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በጥር ወር 2017 ዓ.ም የዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ ይፋ አድርጋለች። በወቅቱ የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከግብርና ሚኒስቴር እና የጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን ፍኖተ ካርታውን በጋራ ይፋ አድርገዋል። ማዕቀፉ ከዚህ ቀደም የነበሩ የዲጂታል ግብርና ኤክስቴንሽንና ማማከር አገልግሎቶች በአንድ ጥላ ስር ያስቀመጠ ነው። ፍኖተ ካርታው የግብርና እሴት ሰንሰለቱን በሙሉ ዲጂታላይዝ የማድረግ አላማ አለው። የማማከርና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ የገበያ መረጃ፣ ዲጂታል ክህሎት፣ ሜካናይዜሽን፣ የዳታ መረጃ አሰባሰብና ዲጂታል መሰረተ ልማት የፍኖተ ካርታው አበይት ትኩረቶች ናቸው። መንግስት ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን የዲጂታል ግብርናን ለማስፋት እየሰራ ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው የዲጂታል ግብርና ጉባኤ በአዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። “ኢኖቬሽን እና የዲጂታል መፍትሄዎችን ለግብርና ዘርፍ በመጠቀም የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ ብሩህ ማድረግ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ኅብረቱ ዲጂታላይዜሽንን የልማት አጀንዳው አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የግብርናው ዘርፍም በዚህ የዲጂታላይዜሽን አህጉራዊ ስትራቴጂ ውስጥ ትኩረት እንደተሰጠው አንስተዋል። ኮሚሽኑ አባል ሀገራት ለዲጂታል ግብርና የመረጃ አጠቃቀምና አስተዳደር አመቺ ፖሊሲዎችን እንዲያዘጋጁ እና እንዲተገብሩ ድጋፍ ያደርጋል ነው ያሉት። ለአርሶ አደሮች፣ ለግብርና ባለሙያዎችና ለወጣቶች በዲጂታል ክህሎቶች ዙሪያ ሥልጠና እንደሚሰጥም አረጋግጠዋል። በአፍሪካ ዲጂታል ግብርናን እውን ለማድረግ የአባል ሀገራት መንግስታት፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች እና የምርምር ተቋማት በቅንጅት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። የአፍሪካ ህብረት የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ በበኩላቸው የአፍሪካን የግብርና ሥርዓት ለመለወጥ እና የምግብ ዋስትናን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ዲጂታል ግብርናን መተግበር የግድ ነው ብለዋል። ዲጂታል ግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የምርት ብክነትን ለመቀነስ፣ የፋይናንስና የገበያ ተደራሽነትን ለማስፋት እንዲሁም የመቋቋም አቅምን ለመገንባት ቁልፍ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ወጣቶች የአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ለኢኖቬሽንና ለዲጂታል ግብርና ትኩረት እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ለማምጣት ዲጂታል ግብርናን እንደ ቁልፍ ስልት መውሰዷንና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ዘርፉን ለማዘመን የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ በመድረኩ የተገኙት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢፋ ሙለታ(ዶ/ር) ገልጸዋል። የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን በስማርት ስልኮች አማካይነት ተደራሽ ማድረግ፣ ትክክለኛ የግብርና መረጃዎችን በአንድ ቋት መያዝና ማዘመን ላይ እየተሰራ መሆኑንና የግብርና ግብዓትን ተደራሽ ማድረግ፣ ከማሳ እስከ ገበያ ባለው ሂደት ውስጥ ያሉ የባለድርሻ አካላትን ቅንጅት ለማጎልበት ዲጂታላይዜሽን ላይ መሰራቱንም ጠቅሰዋል። የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የዲጂታል ግብርና ኤክስቴሽን አገልግሎት፣ የግብርና ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን፣ የገበያ ተደራሽነት፣ የእሴት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የግብርና ምርታማነትን ከአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም መገንባት ጋር ያስተሳሰረ አካሄድን መከተል፣ የግብርና ፖሊሲዎችና የህግ ማዕቀፎች ትግበራ የኮንፍረንሱ ተሳታፊዎች የሚመክሩባቸው አጀንዳዎች ናቸው። ኮንፍረንሱ የእውቀት ሽግግር እና ፖሊሲ ተኮር ውይይቶች የሚደረግበት ሲሆን ስኬታማ የሀገራት የግብርና ኢኒሼቲቮች ለተሳታፊዎች ይቀርቡበታል። በአፍሪካ የዲጂታል ግብርና መፍትሄዎችን ተደራሽነት የሚደግፉ ስትራቴጂዎች የመለየት እና አጋርነቶችን ማጠናከር ከሁነቱ የሚጠበቅ አበይት ውጤት መሆኑን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የኢንተርኔት ተደራሽነት በሚፈለገው መጠን አለማደግ ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ፣ የመሰረ ልማት ግንባታ እና የፖሊሲ ማዕቀፍ የዘርፉ ፈተናዎች ሲሆኑ ለአፍሪካ የዲጂታል ግብርና ትሩፋቶች ከፈተናዎቹ ይገዝፋሉ። ዲጂታል ግብርና ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ኢኮኖመሚ ልማት አንቀሳቃሽ ሞተር የመሆን አቅም አለው።