ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ፤ የመጪው ዘመን የኢኮኖሚ ማንሰራራት መሰረት
Sep 7, 2026 0
አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 2/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ጉልህ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ትገኛለች። ባለፉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ የተደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ተከትሎም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ይፋ መደረጉ ይታወቃል። የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂም ሁሉን አቀፍ እና ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሚመራ ጠንካራ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለመ ነው። ይህም ፈጠራን፣ ምርምርን፣ ስታርት አፕን በማበረታታት፣ የሞባይልና ኢንተርኔት ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር በመጨመር የፋይናንስ አካታችነትን ያረጋገጡ የቴሌብርና መሰል የዲጂታል ክፍያ አማራጮች ማኅበረሰቡ የዕለት ተዕለት አሠራር አካል የሚሆኑበትን ዕድል ፈጥሯል። በፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያና መሶብ የአንድ ማዕከል የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ማዕላትን በማበራከትም የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት ምኅዳርን ፈጥሯል። ይህም የተገልጋዮችን ምልልስ፣ ወጪ፣ ጉልበትና ጊዜ በመቆጠብ፣ የመንግሥት አገልግሎት ውጤታማነትን በማጎልበት እንዲሁም መልካም አስተዳደርን በማስፈን የኢትዮጵያን የብዝኅ ኢኮኖሚ ማንሰራራት ጉዞ እያሳለጠ ይገኛል። በአጠቃላይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የፐብሊክ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት፣ የሰው ኃይል አቅምና ፈጠራን በማጎልበት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማጠናቀቂያና «ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ባስጀመሩበት ወቅት፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የኢትዮጵያን ብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥን መሠረት መጣሉን አስታውሰዋል። የስትራቴጂው ትግበራ ሙሉ በሙሉ በስኬት መጠናቀቁም ለቀጣይ የዲጂታል ኢትዮጵያ አስተማማኝ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ የትኩረት መስክ የብዝኅ ኢኮኖሚ ሥርዓትን በማሳለጥ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማንሰራራት ጉዞ እያነጸ መሆኑን አብራርተዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን በማጎልበት ሁሉም ዜጋ አካታችና ፍትሐዊ የዲጂታል መሠረተ ልማት የሚያገኝበትን ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ለዚህም በስትራቴጂው መሠረት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት፣ የኢንተርኔት ተደራሽነት፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ፣ የዲጂታል ገንዘብ ዝውውርና በተቋማት መካከል የዳታ ልውውጥ ውጤታማነት ለማሻሻል እንደሚሠራ ጠቅሰዋል። የሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ የሳይበር ደኅንነትና የዳታ አስተዳደር ላይ ትኩረት በማድረግ የወጣቶችን የቴክኖሎጂ ክህሎት ማሳደግ፣ አዳዲስ ፈጠራዎችን እና የዲጂታል ሥራ ዕድሎችን ማስፋፋት የስትራቴጂው የትኩረት መስኮች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ዘመኑ የሚጠይቀው ጉዳይ በመሆኑ ኢትዮጵያ በዚህ መስክ ራሷን መቻል እንዳለባትም አስገንዝበዋል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ላይ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ የዲጂታላይዜሽን የትኩረት አቅጣጫ የኢኮኖሚ ማንሰራራት ጉዞውን የሚቀርጽ እመርታዊ ለውጥ አምጥቷል ብለዋል። በዚህም የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ የፈጠራቸው የኢትዮ-ኮደርስ፣ የመሶብ አንድ ማዕከል፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያና የዲጂታል ፋይናንስ ግብይቶች ፈጠራን በማበረታታት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን እያሳለጡ መሆናቸውን አንስተዋል። በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ መሠረተ ልማት ዝርጋታ ጎን ለጎን የዜጎችን ዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ እየተከናወኑ ከሚገኙ ሥራዎች መካከል የኢትዮ-ኮደርስ ሥልጠና ተጠቃሽ ነው። ወጣት ባዩሽ ተስፋዬና ቀለሙ ዘለቀ እንደገለጹት፤ ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን የኮደርስ ሥልጠና መውሰዳቸው የዲጂታል ክህሎታቸውን በማበልጸግ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን ገልጸዋል። ወጣት መሰረት አቦሰጥ እንደምትለውም፤ የኢትዮ-ኮደርስ ሥልጠና የሰው ሠራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅሟን በማጎልበት ተጠቃሚ እያደረጋት ነው። ወጣት እሸቱ አበራ በበኩሉ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና በሌሎች ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ዓይነ ሥውር ዜጎችም እንደ ማንኛውም ሰው የኮደርስ ሥልጠናን መውሰድና ተጠቃሚ በመሆን ከዘመኑ ጋር መራመድ እንደሚችሉ ዕድል መፍጠሩን ገልጿል።    
ማዕከሉ እንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በስፋት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ ነው
Sep 7, 2026 38
አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 2/2018(ኢዜአ)፦መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በስፋት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል ገለጸ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ሥር የሚገኘው የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል፣ መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አሌክስ ደመቀ እንደገለጹት፤ ማዕከሉ አርሶ አደሮችን ለማቋቋም፣ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ገበያ ለማረጋጋት ነው የተቋቋመው፡፡ በአሁኑ ወቅት የደለቡ በሬዎችንና የእንስሳት ተዋጽኦዎችን በማዕከሉ እና በተለያዩ ቦታዎች በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ነው የገለጹት፡፡ በዓሉን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጁ ባዛሮች ላይም ከ350 ሺህ በላይ እንቁላል ማቅረቡን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ በማዕከሉ የተሰማሩ አምራቾች በበኩላቸው መንግሥት ባመቻቸላቸው ዕድል ተጠቅመው ምርቶቻቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።   የእንቁላል አምራች አበራሽ ንጉሤ እንዳሉትም ምርታቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። የወተት ተዋጽኦ አምራቿ ወይዘሮ የሺወርቅ ዳኛቸው ለበዓሉ የሚሆኑ እንደ ቅቤና አይብ ያሉ ምርቶችን ከውጭው ገበያ በቅናሽ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።   ማዕከሉ ከተቋቋመበት ከ2015 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ በእንቁላል ጣይ ዶሮ እርባታ፣ በእንስሳት ማድለብና በወተት ላም እርባታ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ ይገኛል።    
ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ማንሰራራት ሚናውን እያጎለበተ የሚገኘው - የማዕድን ዘርፍ
Sep 7, 2026 90
አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 2/2018(ኢዜአ)፦መንግስት ለማዕድን ዘርፍ ልማት የሰጠው ልዩ ትኩረት እና እየተገኘ ያለው ውጤት ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገቱ ማንሰራራት የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ኢትዮጵያ በርካታ የማዕድን ሀብት ከሚገኝባቸው ሀገራት መካከል አንዷ ብትሆንም ቀደም ባሉት ጊዜያት ሀብቱን በማልማት ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ከማድረግ አንጻር አመርቂ አልነበረም። ባለፉት ዓመታት መንግሥት በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ ማዕድንን አንዱ መሠረታዊ የኢኮኖሚ ልማት ምሰሶ በማድረጉ ዘርፉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ምቹ ምህዳር ተፈጥሯል። የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ ብርሃኔ ያዴሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በመደመር መንግሥት በማዕድን ዘርፍ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች በኢንዱስትሪው እንዲሰማሩ የፖሊሲ እና ምቹ ምህዳር መፍጠር ተችሏል። የማዕድን ዘርፍ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለተኪ ምርት ዕድገት እና የውጭ ምንዛሬን ለማዳን በርካታ ፋይዳዎች እንዳለው አንስተው፤ ባለፉት አመታት ለዘርፉ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል። የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን በስፋት በዘርፉ ማሰማራት የሚያስችሉ አጋዥ የማዕድን ፖሊሲና ህግጋት ተሻሽለው ለማጸደቅ በሂደት ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ቀደም ሲል ማዕድናት በጥሬው ወደ ውጭ ይላኩ እንደነበር አንስተው በአሁኑ ወቅት እሴት ጨምሮ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ማቅረብ ላይ ትኩረት መደረጉንም ገልጸዋል። ለአብነትም በወርቅ፣ በድንጋይ ከሰል፣ ኦፓልና ሌሎች ጌጣጌጦች እሴት ተጨምሮባቸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡበት አሰራር በመፈጠሩ ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል። ባለፉት አራት ዓመታት በወርቅ ዘርፍ የውጭ ምንዛሬ ግኝት ላይ ከፍተኛ ስኬት መገኘቱን አንስተው፤ የወርቅ ማጣሪያ በሀገር ውስጥ እንዲገነባ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። የወርቅ ምርት በ2015 ዓ.ም ከነበረበት 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቶን በ2018 ዓ.ም ወደ 44 ሚሊዮን ቶን ማደጉንና የውጭ ምንዛሬ ግኝቱም ከ196 ሚሊዮን ዶላር ወደ 5 ነጥብ 7 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ማደጉን ተናግረዋል፡፡ በሲሚንቶ ምርትም እንዲሁ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቶን ወደ 10 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቶን በማደግ ከፍተኛ እመርታ ማሳየቱን ገልጸዋል። የድንጋይ ከሰል ምርት ቀደም ሲል በጥሬው ይቀርብ እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ እሴት ተጨምሮበት ወጥ በሆነ ጥራት ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች ግብዓት እስከ 75 በመቶ መሸፈን የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል ቀደም ሲል የሴራሚክ ምርት በአብዛኛው ከውጭ ይገባ እንደነበር አውስተው አሁን ላይ መንግስት ለዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ በሀገር ውስጥ የማምረት አቅም አድጓል ብለዋል። በዚህም በሴራሚክ ምርት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን መሸፈንና ለግዥ ይወጣ የነበረን የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ጨምረው ገልጸዋል።        
በግብርናው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለው ዕመርታዊ ለውጥ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ብስራት ነጋሪ ነው
Sep 7, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ በክልሎች ግብርናውን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሁለንተናዊ ዕድገት ለማምጣት የተጀመረው ጥረት የማንሰራራት ዘመን ብስራት ነጋሪ መሆኑን የተለያዩ ክልሎች የግብርና ቢሮ ኃላፊዎች ገለጹ። ኢትዮጵያ ግብርናውን በመካናይዜሽን፣ በኩታ ገጠም እርሻ፣ እንዲሁም ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ ግብዓቶችን በስፋት በማቅረብ በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ማሳደግ ችላለች። የአሰራር ሥርዓቶችን በማዘመንና እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓይነት ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ በመጠቀም እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ማሳካት የሚያስችል ውጤት ተመዝግቧል። ግብርናው ለኢኮኖሚያዊ ማንሰራራትና ለገጠር መዋቅራዊ ሽግግር ገንቢ ሚና መወጣት የሚችልበትን አቅም ፈጥሯል። በኢትዮጵያ ግብርናውን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሁለንተናዊ ዕድገት ለማምጣት የተጀመረው ጥረት የማንሰራራት ዘመን ብስራት ነጋሪ ነው። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር ለኢዜአ እንዳሉት፤ መሬት፣ ጊዜ፣ ጉልበት እና ሀሳብን አቀናጅቶ በመጠቀም በሰብል ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል። በዚህም በክልሉ በ2018 ወደ 1 ነጥብ 28 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በሰብል በመሸፈን፤ አጠቃላይ የሰብል ምርት መጠኑን ከ161 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማድረስ ተችሏል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ የሰብል ብዝሃነትን በማስፋት ከውጭ የሚገባውን ምርት የሚተኩ፣ ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ማምረት መጀመራቸውን ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ማስረሻ በላቸው፤ በክልሉ "የማይታረስ መሬት ሊኖር አይገባም" በሚል በድግግሞሽ የሚታረሰውን መሬት ከ560 ሺህ ሄክታር ወደ 801 ሺህ ሄክታር በማሳደግ የኢትዮጵያን የማንሰራራት ዘመነ ለማብሰር መሰረት የሚጥሉ ውጤቶች መመዝገባቸው ገልጸዋል። በሆርቲካልቸር ልማት ከ41 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን በመግለጽ፤ ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለዓለም ገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ተገኝቷል ብለዋል። በሌማት ትሩፋት ሥራዎችን ለማጠናከር የመኖ ማሽኖች ተከላ፣ የዓሳ ዕርባታ ማዕከላት ግንባታ፣ የዶሮ ማቆያና መሰል ማስፋፊዎችን እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የምክትል ቢሮ ኃላፊ አጀበ ስንሻው በበኩላቸው፤ በክልሉ የግብርና ሜካናይዜሽን በማስፋት 1 ነጥብ 4 ሚሊዬን ሄክታር መሬት በትራክተር ይታረሳል ብለዋል። ለአርሶ አደሩ 7 ነጥብ 1 ሚሊዬን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እና ከ 310 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር በማቅረብ የአቅርቦትን ማሻሻልና የታቀደውን የግብርና ግብዓት ማሳካት መቻላቸውን ገልጸዋል። በኩታ ገጠም እርሻ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ፣ ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብ እና ለውጭ ገበያ የሚቀርበን ምርት ማሳደግ የሚያስችል ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።      
ኢትዮጵያ የንጹህ ኃይል ልማቷን አጠናክራ ትቀጥላለች - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Sep 7, 2026 84
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የንጹህ ኃይል ልማቷን አጠናክራ በመቀጠል ለጎረቤት ሀገራት የምታቀርበውን የኃይል መጠን ለማሳደግ እየሰራች መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ዱባይ እየተካሄደ ባለው ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ጉባኤ (AIM Congress) ላይ ንግግር አድርገዋል።   ፕሬዝዳንት ታዬ ለታዳሚዎች ባስተላለፉት መልዕክት፤ ጉባኤው የዓለም ኢኮኖሚ መዋቅር በመሰረታዊነት እየተለወጠና የቴክኖሎጂ ለውጦች አጠቃላይ ሁኔታዎችን እየቀየረ ባለበት ጊዜ መካሄዱ ጠቃሚ ያደርገዋል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ተለዋዋጭ የጂኦ ፖለቲካ ሁኔታዎች የዓለምን የንግድ የእሴት ሰንሰለት እየወሰነ መምጣቱን ገልጸው፤ እነዚህ አዲስ ክስተቶች በማደግ ላይ ላሉ ሀገሮች በተለይም ለአፍሪካ ካመጡት ችግር ባልተናነሰ ወደ ውስጥ ለመመልከት ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል። ይህንንም ተከትሎ የአፍሪካ አገራት በአፍሪካ ኅብረት በኩል የዚህ ተለዋዋጭ ዓለም ክስተት ተመልካች ሳይሆኑ ዋነኛ ተሳታፊና ሥርዓት ገንቢ አካል ለመሆን የጋራ መግባባት መደረሱን ተናግረዋል። በተለይም ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት እየተገበረቻቸው ያሉትን ተከታታይ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራሞች ከዚህ አኳያ የተቃኙ መሆናቸውን አብራርተዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ እንደገለጹት፤ አፍሪካ ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚ እንድትገነባ ያላትን የስትራቴጂክ ኢንቨስትመንት ዕድሎች አሟጣ ለመጠቀም አምስት ዋና ዋና ጉዳዮችን ማከናወን ይጠበቅባታል። አንደኛ በአፍሪካ የጋራ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ለማምጣት በንጹህ የኤሌትሪክ ኃይል ማስፋፋት ላይ ትኩረት ሊያደርጉ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ ሀገሮች በተለይም ከንፋስ፣ ከፀሐይ፣ ከአንፋሎትና ከኃይድሮ ኤሌክትሪክ ልማት ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያም የንጹህ የኃይል አማራጭን እንደ ሀገራዊ ሃብት ብቻ ሳይሆን ለፈጣን የኢኮኖሚ እድገት መሰረት አድርጋ ትወስደዋለች ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ከንጹህ ሃይል ብቻ 60 ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌትሪክ ሃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት ገልጸው፤ እኤአ 2030 ኢትዮጵያ 13 ሺህ ሜጋ ዋት ለማመንጨት እቅድ እንዳላት ተናግረዋል። በዚህም ለምስራቅ አፍሪካና ለሌሎች አገሮች የሚቀርበውን የኃይል አቅርቦት ለማሳደግ እንደምትሰራም ጠቁመዋል። በሁለተኛ ደረጃ የአፍሪካ አገራት በግብርና ዘርፍ ላይ መሥራት እንዳለባቸው ተናግረው፤ ኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተለይም በስንዴ ምርት ዘርፍ ያስመዘገበችውን እመርታ በተሞክሮ ለታዳሚው አቅርበዋል።   በሦስተኛ ደረጃ የአፍሪካ አገሮች ከወርቅ ጀምሮ እስከ ኮባልትና ሊቲየም ድረስ ያላቸውን የተለያዩ የማዕድን ሀብቶች መጠቀም እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ታንታለም የተባለውን ማዕድን በማምረት በዓለም ስድስተኛ ደረጃ መያዟን ገልጸዋል። የአፍሪካ አገሮች ለዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት የመሰረተ ልማት ግንባታና የዲጂታል መሰረተ ልማት ማስፋፋት ላይ ትኩረት አድርገው መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚሰራውን ሥራ ለአብነት ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋነኛ የትስስር ማዕከልነቷን ለማፅናት የሚያስችላትን የቢሾፍቱ አየር መንገድ በ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር እየገነባች መሆኑን አስረድተዋል። በሌላ በኩል ሦስት ነጥብ አራት ትሪሊዮን ዶላር የሚጠጋ የአገራት አጠቃላይ አገራዊ ምርት የገበያ አቅም ያለው የአፍሪካ ነጸ የንግድ ቀጣና የመሰሉ ፕሮጀክቶች ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተናግረዋል። በአምስተኛ ደረጃ የአፍሪካ አገራት ያላቸውን የሰው ኃይል በአግባቡ ሊጠቀሙ እንደሚገባ አስገንዘበው፤ ኢትዮጵያ በተለይም በዲጂታል ቴክኖሎጂው ክህሎት ወጣቶች ያላቸውን አቅም ለማጎልበት የኮደር ሥልጠና እየሰጠች መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህ ኢኒሼቲቭ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰው፤ ለዚህም ምስጋና አቅርበዋል። የተለያዩ የአገራት መሪዎች፣ የኢንቨስትመንት ኩባንያዎች ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የምርምር ተቋማት ተወካዮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ዛሬ በዱባይ የተጀመረው ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክሮ ከነገ በስትያ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
የሚታይ
በግብርናው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለው ዕመርታዊ ለውጥ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ብስራት ነጋሪ ነው
Sep 7, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ በክልሎች ግብርናውን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሁለንተናዊ ዕድገት ለማምጣት የተጀመረው ጥረት የማንሰራራት ዘመን ብስራት ነጋሪ መሆኑን የተለያዩ ክልሎች የግብርና ቢሮ ኃላፊዎች ገለጹ። ኢትዮጵያ ግብርናውን በመካናይዜሽን፣ በኩታ ገጠም እርሻ፣ እንዲሁም ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ ግብዓቶችን በስፋት በማቅረብ በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ማሳደግ ችላለች። የአሰራር ሥርዓቶችን በማዘመንና እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓይነት ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ በመጠቀም እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ማሳካት የሚያስችል ውጤት ተመዝግቧል። ግብርናው ለኢኮኖሚያዊ ማንሰራራትና ለገጠር መዋቅራዊ ሽግግር ገንቢ ሚና መወጣት የሚችልበትን አቅም ፈጥሯል። በኢትዮጵያ ግብርናውን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሁለንተናዊ ዕድገት ለማምጣት የተጀመረው ጥረት የማንሰራራት ዘመን ብስራት ነጋሪ ነው። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር ለኢዜአ እንዳሉት፤ መሬት፣ ጊዜ፣ ጉልበት እና ሀሳብን አቀናጅቶ በመጠቀም በሰብል ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል። በዚህም በክልሉ በ2018 ወደ 1 ነጥብ 28 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በሰብል በመሸፈን፤ አጠቃላይ የሰብል ምርት መጠኑን ከ161 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማድረስ ተችሏል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ የሰብል ብዝሃነትን በማስፋት ከውጭ የሚገባውን ምርት የሚተኩ፣ ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ማምረት መጀመራቸውን ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ማስረሻ በላቸው፤ በክልሉ "የማይታረስ መሬት ሊኖር አይገባም" በሚል በድግግሞሽ የሚታረሰውን መሬት ከ560 ሺህ ሄክታር ወደ 801 ሺህ ሄክታር በማሳደግ የኢትዮጵያን የማንሰራራት ዘመነ ለማብሰር መሰረት የሚጥሉ ውጤቶች መመዝገባቸው ገልጸዋል። በሆርቲካልቸር ልማት ከ41 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን በመግለጽ፤ ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለዓለም ገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ተገኝቷል ብለዋል። በሌማት ትሩፋት ሥራዎችን ለማጠናከር የመኖ ማሽኖች ተከላ፣ የዓሳ ዕርባታ ማዕከላት ግንባታ፣ የዶሮ ማቆያና መሰል ማስፋፊዎችን እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የምክትል ቢሮ ኃላፊ አጀበ ስንሻው በበኩላቸው፤ በክልሉ የግብርና ሜካናይዜሽን በማስፋት 1 ነጥብ 4 ሚሊዬን ሄክታር መሬት በትራክተር ይታረሳል ብለዋል። ለአርሶ አደሩ 7 ነጥብ 1 ሚሊዬን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እና ከ 310 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር በማቅረብ የአቅርቦትን ማሻሻልና የታቀደውን የግብርና ግብዓት ማሳካት መቻላቸውን ገልጸዋል። በኩታ ገጠም እርሻ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ፣ ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብ እና ለውጭ ገበያ የሚቀርበን ምርት ማሳደግ የሚያስችል ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።      
ኢትዮጵያ የንጹህ ኃይል ልማቷን አጠናክራ ትቀጥላለች - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Sep 7, 2026 84
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የንጹህ ኃይል ልማቷን አጠናክራ በመቀጠል ለጎረቤት ሀገራት የምታቀርበውን የኃይል መጠን ለማሳደግ እየሰራች መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ዱባይ እየተካሄደ ባለው ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ጉባኤ (AIM Congress) ላይ ንግግር አድርገዋል።   ፕሬዝዳንት ታዬ ለታዳሚዎች ባስተላለፉት መልዕክት፤ ጉባኤው የዓለም ኢኮኖሚ መዋቅር በመሰረታዊነት እየተለወጠና የቴክኖሎጂ ለውጦች አጠቃላይ ሁኔታዎችን እየቀየረ ባለበት ጊዜ መካሄዱ ጠቃሚ ያደርገዋል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ተለዋዋጭ የጂኦ ፖለቲካ ሁኔታዎች የዓለምን የንግድ የእሴት ሰንሰለት እየወሰነ መምጣቱን ገልጸው፤ እነዚህ አዲስ ክስተቶች በማደግ ላይ ላሉ ሀገሮች በተለይም ለአፍሪካ ካመጡት ችግር ባልተናነሰ ወደ ውስጥ ለመመልከት ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል። ይህንንም ተከትሎ የአፍሪካ አገራት በአፍሪካ ኅብረት በኩል የዚህ ተለዋዋጭ ዓለም ክስተት ተመልካች ሳይሆኑ ዋነኛ ተሳታፊና ሥርዓት ገንቢ አካል ለመሆን የጋራ መግባባት መደረሱን ተናግረዋል። በተለይም ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት እየተገበረቻቸው ያሉትን ተከታታይ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራሞች ከዚህ አኳያ የተቃኙ መሆናቸውን አብራርተዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ እንደገለጹት፤ አፍሪካ ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚ እንድትገነባ ያላትን የስትራቴጂክ ኢንቨስትመንት ዕድሎች አሟጣ ለመጠቀም አምስት ዋና ዋና ጉዳዮችን ማከናወን ይጠበቅባታል። አንደኛ በአፍሪካ የጋራ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ለማምጣት በንጹህ የኤሌትሪክ ኃይል ማስፋፋት ላይ ትኩረት ሊያደርጉ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ ሀገሮች በተለይም ከንፋስ፣ ከፀሐይ፣ ከአንፋሎትና ከኃይድሮ ኤሌክትሪክ ልማት ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያም የንጹህ የኃይል አማራጭን እንደ ሀገራዊ ሃብት ብቻ ሳይሆን ለፈጣን የኢኮኖሚ እድገት መሰረት አድርጋ ትወስደዋለች ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ከንጹህ ሃይል ብቻ 60 ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌትሪክ ሃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት ገልጸው፤ እኤአ 2030 ኢትዮጵያ 13 ሺህ ሜጋ ዋት ለማመንጨት እቅድ እንዳላት ተናግረዋል። በዚህም ለምስራቅ አፍሪካና ለሌሎች አገሮች የሚቀርበውን የኃይል አቅርቦት ለማሳደግ እንደምትሰራም ጠቁመዋል። በሁለተኛ ደረጃ የአፍሪካ አገራት በግብርና ዘርፍ ላይ መሥራት እንዳለባቸው ተናግረው፤ ኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተለይም በስንዴ ምርት ዘርፍ ያስመዘገበችውን እመርታ በተሞክሮ ለታዳሚው አቅርበዋል።   በሦስተኛ ደረጃ የአፍሪካ አገሮች ከወርቅ ጀምሮ እስከ ኮባልትና ሊቲየም ድረስ ያላቸውን የተለያዩ የማዕድን ሀብቶች መጠቀም እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ታንታለም የተባለውን ማዕድን በማምረት በዓለም ስድስተኛ ደረጃ መያዟን ገልጸዋል። የአፍሪካ አገሮች ለዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት የመሰረተ ልማት ግንባታና የዲጂታል መሰረተ ልማት ማስፋፋት ላይ ትኩረት አድርገው መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚሰራውን ሥራ ለአብነት ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋነኛ የትስስር ማዕከልነቷን ለማፅናት የሚያስችላትን የቢሾፍቱ አየር መንገድ በ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር እየገነባች መሆኑን አስረድተዋል። በሌላ በኩል ሦስት ነጥብ አራት ትሪሊዮን ዶላር የሚጠጋ የአገራት አጠቃላይ አገራዊ ምርት የገበያ አቅም ያለው የአፍሪካ ነጸ የንግድ ቀጣና የመሰሉ ፕሮጀክቶች ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተናግረዋል። በአምስተኛ ደረጃ የአፍሪካ አገራት ያላቸውን የሰው ኃይል በአግባቡ ሊጠቀሙ እንደሚገባ አስገንዘበው፤ ኢትዮጵያ በተለይም በዲጂታል ቴክኖሎጂው ክህሎት ወጣቶች ያላቸውን አቅም ለማጎልበት የኮደር ሥልጠና እየሰጠች መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህ ኢኒሼቲቭ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰው፤ ለዚህም ምስጋና አቅርበዋል። የተለያዩ የአገራት መሪዎች፣ የኢንቨስትመንት ኩባንያዎች ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የምርምር ተቋማት ተወካዮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ዛሬ በዱባይ የተጀመረው ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክሮ ከነገ በስትያ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ በመቀየስ ረገድ መሪ ሚና መጫወት ይገባታል-ክላቨር ጋቴቴ
Sep 7, 2026 127
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ አፍሪካ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ድርድሮችና መፍትሔዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የጎላ ሚና መጫወት እንዳለባት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ፡፡ 14ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። ጉባኤው "ከተስፋ ቃል ወደ ተግባር፤ የቤሌም-አንታልያ-አዲስ አበባ ፍኖተ ካርታ" በሚል መሪ ሐሳብ ነው እየተካሄደ ያለው። የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክላቨር ጋቴቴ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፣ አፍሪካ ለዓለም አቀፍ የካርቦን ልቀት የምታበረክተው አስተዋጽኦ አራት በመቶ ቢሆንም የችግሩን ከባድ መዘዝ እየተሸከመች ትገኛለች። ሆኖም ይህ እውነታ ለአፍሪካ የተጎጂነት ታሪክ ብቻ ሆኖ ሊቀጥል እንደማይገባ ተናግረው አፍሪካ ያላትን ከፍተኛ የታዳሽ ኃይል አቅም፣ የማዕድን ሀብቶች፣ ወጣት የሰው ኃይል እና እያደገ ያለውን ገበያ በመጠቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ መፍትሔዎችን በመቀየስ ረገድ መሪ ሚና መጫወት እንዳለባት ገልጸዋል። አፍሪካ እስከ እ.ኤ.አ 2030 ድረስ የተቀመጡ የአየር ንብረት ግቦችን ለመተግበር በየዓመቱ 277 ቢሊዮን ዶላር የሚያስፈልጋት ቢሆንም እያገኘች ያለችው ከፍላጎቷ 11 በመቶ ያህሉን ብቻ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት እርምጃዎች ከኃይል ተደራሽነት፣ከኢንዱስትሪ ልማት እና ከሥራ እድል ፈጠራ ጋር ተያይዘው መከናወን እንዳለባቸው አሳስበዋል። ከ600 ሚሊዮን በላይ አፍሪካውያን አሁንም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ያላገኙ በመሆናቸው የታዳሽ ኃይልን ማስፋፋት የኢኮኖሚው መሠረት ሊሆን ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣናን በመጠቀም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ሀብቶች ላይ እሴት በመጨመር አህጉራዊ የእሴት ሰንሰለት መገንባት ይቻላል ሲሉም ገልጸዋል።
የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 7, 2026 171
አዲስ አበባ ፤ጳጉሜን 2/2018(ኢዜአ)፦ በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማንሠራራት ቀንን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ቀደም ሲል “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ሲባል የነበረው ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ የተረጋገጠ እውነት መሆኑን ተናግረዋል። ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል ብለዋል። ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን ብለዋል። #EthiopiaDelivers
በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት ልዑክ ዱባይ ገባ
Sep 6, 2026 373
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፦በኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት ልዑክ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ጉባኤ (AIM Congress) ላይ ለመሳተፍ ዛሬ ማምሻውን ዱባይ ገብቷል። በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተመራው ልዑክ ዱባይ ሲደርስ በአገሪቷ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው የኢዜአ ሪፖርተር ከሥፍራው ዘግቧል። የኢንቨስትመንት ጉባኤው ከነገ ጳጉሜን 2 እስከ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት በዱባይ ዓለም አቀፍ የንግድ ማዕከል ይካሄዳል። እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2011 የተቋቋመው ይህ የኢንቨስትመንት ጉባዔ ውጤታማ የኢንቨስትመንት የማስተዋወቂያ ስትራቴጂዎችን በማሳደግና ለኢኮኖሚ ምርታማነት እድሎችን በማመቻቸት የዓለምን ኢኮኖሚ ለማጎልበት የሚሰራ የኤም ግሎባል ፋውንዴሽን ኢንሼቲቭ ነው።   በየዓመቱ የሚካሄደው ይህ ዓለም አቀፍ ጉባኤ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስፋት፣ በአገራት መካከል አጋርነትና የኢኮኖሚ ትብብርን በማጠናከር እንዲሁም በመስኩ የሚስተዋሉ ችግሮችን እልባት በመስጠት በመካከለኛው ምስራቅ ዋነኛ የኢንቨስትመንት መድረክም ሆኖ እያገለገለ ነው። በጉባኤው የአገራት መሪዎች፣ በተለያዩ የዓለም አገራት የሚገኙ ግዙፍ የቢዝነስና ተቋማት ሥራ አስፈጻሚዎች፣ፖሊሲ አውጪዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች፣ የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት ተወካዮች፣ሌሎች የዘርፉ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በመድረኩ በጋራ ይመክሩበታል። በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች መንግሥት ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ዘንድሮ ለ15ኛ ጊዜ በሚካሄደው በዚሁ የዱባይ ጉባኤ ታዳሚዎች በዲጂታል ኢኮኖሚ፣ በዘላቂ ልማትና በስትራቴጂያዊ አጋርነት ላይ ትኩረት አድርገው ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህንንም ተከትሎ መድረኩ የዓለምን ኢኮኖሚ ለማጠናከር የሚያስችሉ ውጤታማ ውይይቶችና ግዙፍ የኢንቨስትመንት ስምምነቶች እንደሚያደረጉ ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶታል። ኢትዮጵያ በአገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በተለይም የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሣብና የኢኮኖሚ ትብብሮችን በማጠናከር የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ለማሣደግና ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ እየሠራች ነው።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ከሀገራዊ ምክክሩ የተገኙ ምክረ-ሃሳቦች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባሉ
Sep 7, 2026 138
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ ከሀገራዊ ምክክሩ የተገኙ ምክረ-ሃሳቦች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርቡ ምክር ቤቱ ገልጿል። ከሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የተገኙ ምክረ- ሃሳቦች በየፈርጁ እየተደራጁ መሆኑንና በቀጣይ ምክረ-ሃሳቦቹን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ የኮሚሽኑ መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦ ኮሚሽኑ ከሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የተገኙ ምክረ-ሃሳቦችን በየፈርጁ በማደራጀት ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 01 ቀን - ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን ሲያስተባብር መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ኮሚሽኑ በርካታ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ምክረ-ሃሳቦች ማሰባሰብ የቻለ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያዊያን በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ለመመካከር ያሳዩት ቁርጠኝነት ውጤት ነው፡፡ ኮሚሽኑ በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 አንቀፅ 9 (10፣ 11፣ 12) በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ አጀንዳዎችን፣ የምክክሮቹን ሂደት፣ በምክክሮቹ የተገኙ ምክረ-ሃሳቦችን እንዲሁም ምክረ- ሃሳቦቹ በተግባር ላይ ሊውሉ የሚችሉበትን ሥልት የሚገልጽ ሰነድ በማዘጋጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለአስፈጻሚ አካሉ እና ለሌሎች የሚመለከታቸዉ የመንግስት አካላት አቅርቦ፤ ለሕዝብም ይፋ እንደሚያደርግ፤ መንግሥት ከሀገራዊ ውይይቶች የሚገኙ ምክረ-ሃሳቦችን በተግባር ላይ ለማዋል እንዲችል ግልፅ እና ተጨባጭ የሆነ ዕቅድ እንዲዘጋጅ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ፤ እንዲሁም የምክረ-ሃሳቦቹን አፈፃፀም መከታተል የሚያስችል ሥርዓት እንደሚዘረጋ በአዋጁ ተደንግጓል፡፡ ይህንን መነሻ በማድረግ ኮሚሽኑ፦ በአሁኑ ሰዓት ከሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የተገኙ ምክረ-ሃሳቦችን በየፈርጁ በማደራጀት ላይ ይገኛል፤ በቀጣይ ምክረ-ሃሳቦቹን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል፤ በመቀጠልም ምክረ-ሃሳቦቹን አግባብነት ባለው መንገድ ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል፤ በመጨረሻም ምክረ-ሃሳቦቹን ለአስፈፃሚ በማቅረብ ተፈፃሚነታቸውን ይከታተላል፡፡
የመንግሥት አዳዲስ እሳቤዎች በተለያዩ መስኮች የሚጨበጡ እመርታዎች እንዲመዘገቡ አድርገዋል - የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Sep 6, 2026 412
አዳማ ፤ ጳጉሜን 01/2018 (ኢዜአ) ፦ ያለፉት ዓመታት በመንግሥት አዳዲስ እሳቤዎችና በህዝቡ ትብብር በተለያዩ መስኮች የሚታዩና የሚጨበጡ እመርታዎች መመዝገባቸውን የተለያዩ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ወደ አዲስ ዓመት በሚደረገው ሽግግር የጳጉሜን 1 'የእመርታ ቀን' አስመልክተው ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ምክትል ሰብሳቢ አቶ በየነ ደሳለኝ፤ የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች መከበራቸው ሀገሪቱ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች በማንሳት ቀጣይ ስንቅ ለማድረግ የሚያነሳሳ ይሆናል ብለዋል። መንግሥት ባለፉት ዓመታት በሀገር በቀል እሳቤዎችና ፖሊሲዎች ሀገራዊ አቅሞችን መጠቀም ያስቻሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችንና በርካታ የልማት ኢንሼቲቮችን በመተግበር አስደናቂ እመርታዎች ማስመዝገቡን አንስተዋል። በተለይም በግብርናው ዘርፍ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ላይ የመጣው ለውጥ እና የታየው ስኬት ሊደነቅ የሚገባው ነው ብለዋል። የተለያዩ የግብርና ኢንሼቲቮች የተረጂነትና የጠባቂነት አስተሳሰብን በማስወገድ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆኑንም አንስተዋል። በሌሎችም ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችም እመርታ የተመዘገበባቸውና አመርቂ ውጤት የተገኘባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በድምሩ ባለፉት ዓመታት በመንግሥት አዳዲስ እሳቤዎችና በህዝቡ ትብብር በተለያዩ መስኮች የሚታዩና የሚጨበጡ እመርታዎች የተመዘገቡበት መሆኑን ተናግረዋል። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ሥራ አስፈጻሚ እና የኦሮሚያ ክልል አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ ተሰማ፤ በመንግሥት ሀገር በቀልና አዳዲስ እሳቤዎች በመታገዝ ባለፉት ጥቂት አመታት አስደናቂ ውጤት መመዝገቡን ተመልክተናል ብለዋል። የውጭ ምንዛሪ እጥረትንና የዋጋ ግሽበትን በመቋቋም ጭምር የሀገሪቱን ገጽታ የቀየሩ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን በጥራት እና በፍጥነት በመፈጸም የላቀ እመርታ መታየቱንም አንስተዋል። በጥናት ላይ ተመስርቶ በሀገሪቱ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ መደረጉ ለዜጎች ሰፊ የስራ እድልን ከመፍጠር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ወጪን በመቀነስ ረገድ ትርጉም ያለው ስራ ተሰርቷል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የምሥራቅ ሸዋ ዞን አስተባባሪ ወይዘሮ ሠናይት በላይ፤ በአዲሱ ዓመት መባቻ ላይ የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች መከበራቸው በጎ ሀሳቦችን እንድናፈልቅ ልዩ ስሜት እንዲፈጠርብን ያደርጋል ብለዋል። መንግሥት በጥቂት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር በተለይም በመስኖ ስንዴን በማልማት ከሀገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሉ ትልቅ እመርታ መሆኑን ገልጸዋል። በቱሪዝም፣ ዲጂታላይዜሽን፣ የአረንጓዴ አሻራ ልማት፣ በአትክልትና ፍሬፍሬ ልማት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች እመርታ መመዝገቡን ማየት ችለናል ብለዋል።
የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 6, 2026 429
አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 1 /2018 (ኢዜአ)፦የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእመርታ ቀንን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት፣አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል ብለዋል። ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል ነው ያሉት። በ "ሌማት ትሩፋት" የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን በማለት ገልፀዋል። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች መሆናቸውን ጠቁመዋል። ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው ብለዋል። #EthiopiaDelivers
ኢጋድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባውን ሊያደርግ ነው
Sep 6, 2026 436
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት 74ኛው አስቸኳይ ስብሰባውን መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም በጅቡቲ ያካሂዳል። በስብሰባው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች ይሳተፋሉ። በቀጣናው ሰላም እና ጸጥታ እንዲሁም በሌሎች አበይት ጉዳዮች ላይ ምክክር ይደረጋል። ይህ ስብሰባ አባል ሀገራት በቀጣናው ያለውን የጸጥታና የደህንነት ሁኔታ እና እየተከናወኑ ያሉ ቀጣናዊ ጥረቶችን በመገምገም ለሰላም፣ መረጋጋትና ትብብር ያላቸውን የጋራ አቋም እንዲያጠናክሩ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ የድርጅቱን ተልዕኮ እና በቀጣናው ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ላይ የሚያደርገውን ድጋፍ እና የኢጋድ ስምምነትን (IGAD Treaty) ተፈጻሚነት ማጠናከርን ጨምሮ በዋና ዋና ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል። ስብሰባው የኢጋድ አባል ሀገራት በቀጣናው የሚገኙ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመቅረፍ እንዲሁም ለሕዝቦቻቸው ሰላም፣ መረጋጋትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡበት እንደሆነም ተገልጿል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከኢጋድ ቁልፍ የፖሊሲ አደረጃጀቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ የድርጅቱን ሥራዎች በመምራትና በአባል ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና የሚጫወት ነው።
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!
Sep 6, 2026 432
እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል፤ በዚያ አግባብ የሚመጣ መሻሻል ከታለመዉ ግብ ለመድረስ የትውልዶችን ጥረት የሚጠይቅ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ግን በቁጭት ለዘመናት ከቆየንበት ኋላ ቀርነት እና ድህነት በአዝጋሚ ጉዞ ለመላቀቅ ስለማይቻል እመርታዊ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርገን ሠርተን ስኬቶችን እያስመዘገብን ነው፡፡ ያለፉት ጥቂት ዓመታት ጥረቶቻችን ውጤቶች የሚያሳዩትም ይህንኑ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ጀርባ ያጎበጡ የውጭ ዕዳዎችን ጫና በመቀነስ፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፣ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅም በማሻሻል፣ የማዕድን ሀብቶች አጠቃቀምን በማላቅ እመርታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡ የመንግሥት አጠቃላይ የማድረግ ዐቅም በእጅጉ ተለውጧል፡፡ ይህንን እመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ የተቻለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በማድረግ፤ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል፤ የዜጎችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በማሳደግ፤ የቢዝነስ ሥርዐቱን ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ፤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ዐቅም ከዜጋ ተኮር እና ብሔራዊ ጥቅም አንጻር በመግራት የመደመር መንግሥት ባደረገዉ ሰፊ ጥረት ነው፡፡ ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ የኃላፊነት ስሜት በሕጋዊ አግባብ መጠቀም ጀምራለች፤ ታዳሽ ኃይልን በማምረት ከራስ አልፎ ለቀጠናዉ የኃይል ምንጭ ኾናለች፤ ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በመተግበር ኹለንተናዊ ዕድገቶችን እያስመዘገበች መጥታለች፤ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በዓለም ገበያ ተወዳድራ የመሸጥ ዐቅም ፈጥራለች፡፡ የመንግሥት የልማት ዕቅድ ከቁጥ ቁጥ ወጥቶ ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ግብ አስቀምጦ እየተተገበረ ነው፡፡ በ2018 ዓ/ም በሁሉም መስክ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ለውጥ የመሸጋገር ሀገራዊ ራዕይን ማሳካት ተችሏል፡፡ ኢትዮጵያን በ2023 ዓ.ም አፍሪካዊት የብለጽግና ተምሳሌት የማድረግ ግብ ተቀምጦ ርብርብ እየተደረገ የስኬቱ ዋዜማ እየተቃረበ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመደመር መንግሥት በተነደፉ የፖሊሲ ሐሳቦች ኹለንተናዊ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዞን ጀምራለች፡፡ በገቢ አሰባሰብ ላይ የታየዉ እመርታ አንዱ አብነት ነው፡፡ የግብር እና ታክስ መሠረትን በማስፋት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፤ የግብር ከፋዩን የመንግሥት አገልግሎት እርካታ በመሶብ አንድ ማእከል እና በዲጂታል አገልግሎቶች ከፍ በማድረግ የላቀ አፈጻጸም ማሳየት ተችሏል፡፡ በዚህም የበጀት ጉድለትን በእጅጉ ማጥበብ ተችሏል፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የመንግሥት ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ዐቅም በእጅጉ አድጓል፡፡ ፕሮጀክቶች መቼ እንደሚጀመሩ እና በምን ያህል በጀት እንደሚፈጸሙ ብቻ ሳይኾን መቼ ተጠናቅቀው በትክክል አገልግሎት እንደሚሰጡ ጭምር በከፍተኛ የራስ መተማመን የመሠረት ድንጋይ ሲቀመጥ መናገር የሚቻልበት ቁመና ላይ ተደርሷል፡፡ እመርታዊ ስኬቶችን ዕውቅና ለመስጠት፣ በቀጣዮቹም ዓመታት የበለጠ እመርታዊ ስኬቶችን ለማስመዝገብ መዘጋጀት አስፈላጊ በመኾኑ ዛሬ ጳጒሜን 01 ቀንን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት!” በሚል መሪ መልእክት እያከበርን ነው፡፡ እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን! ጳጒሜን 01 ቀን 2018 ዓ.ም የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ በዓባይ ውሃ አጠቃቀም ላጣቻቸው የልማት ዕድሎችና ለደረሰባት ታሪካዊ በደል ማካካሻ የመጠየቅ ሕጋዊና ተፈጥሯዊ መብት አላት
Sep 5, 2026 659
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 30/2018 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ውሃ አጠቃቀም ላጣቻቸው ሰፊ የልማት ዕድሎች፣ ለደረሰባት ታሪካዊ በደልና ለተፈጸመባት ኢ-ፍትሐዊ ግፍ ተገቢውን ማካካሻ የመጠየቅ ሕጋዊ፣ ተፈጥሯዊና ኢኮኖሚያዊ መብት እንዳላት የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች የቀድሞ ሚኒስትር ዴኤታ ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር) ገለጹ። ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር) የምስራቅ አፍሪካ ፖሊሲ ምርምር ኢንስቲትዩት መስራችና የቀድሞው ምክትል ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች የቀድሞ ሚኒስትር ዴኤታ ናቸው። ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ለዓባይ ወንዝ ከምታመነጨው ከፍተኛ የውሃ ድርሻ አኳያ ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ ሃብት አጠቃቀም እንዲሰፍን ስትታገል ቆይታለች። ኢትዮጵያ ለዓባይ ወንዝ የምታበረክተው ከፍተኛ የውሃ ድርሻና በታሪክ በነበራት ዝቅተኛ የውሃ አጠቃቀም መካከል ያለው አለመጣጣምና ልዩነት የፍትሐዊ ተጠቃሚነት መሰረታዊ ጥያቄን የሚያስነሳ ነው ብለዋል። በዓባይ ወንዝ ላይ ለዘመናት የቆየው ኢ-ፍትሐዊ የውሃ ሃብት አጠቃቀም ውስንነትም የታሪክ እርማትና ካሳም ጭምር የሚያስፈልገው ሕጋዊና ፍትሐዊ መሰረት ያለው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ከ86 በመቶ በላይ የዓባይ ውሃ ምንጭ ኢትዮጵያ ሆና ሳለ ምንም ሳትጠቀም፣ ግብፅ በአንጻሩ 85 በመቶ የወንዙን የውሃ ሃብት ስትጠቀም ቆይታለች ብለዋል። በዚህ መነሻነትም ኢትዮጵያ እስካሁን ለደረሰባት ታሪካዊና ኢ-ፍትሐዊ ኪሳራ ግልፅ ማካካሻ የመጠየቅ ሕጋዊና ፍትሐዊ መብት እንዳላት አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ በዓባይ ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባታል ያሉት ብርሃኑ (ዶ/ር)፤ የሥነ-ምኅዳር ሚዛን ለመጠበቅ ለምታበረክተው የልማት አስተዋጽኦ ካሳ ያስፈልጋታል ብለዋል። በቀጣይም ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ሕጋዊ ካሳ በአረንጓዴ ዐሻራና ሥነ-ምኅዳር ጥበቃ፣ የደን ልማትና ለታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት በምታበረክተው አስተዋጽኦ ልክ መታየት እንደሚኖርበት አብራርተዋል። የታችኛው የተፋሰሱ ሀገራትም ወንዙን ለመጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርጋቸውን ሁለንተናዊ የአረንጓዴ ልማት የመደገፍ ግዴታ ጭምር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ዓባይን ባለመጠቀሟ ብዙ የልማት ዕድል አምልጧታል ያሉት ብርሃኑ (ዶ/ር)፤ ይህም ሳይበቃ ግብፅ ወንዙን በብቸኝነት ከመጠቀም ባሻገር የኢትዮጵያ የግጭቶች ምንጭ ሆና ዘልቃለች ብለዋል። ግብፅ በጫካ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂና የሽብር ኃይሎችን በቁሳቁስ በመደገፍ ኢትዮጵያ በውክልና ጦርነት እንድትቆይ በማድረግ የባሕር መግቢያና መውጫ በሯን ጭምር እንዳሳጣቻት አስታውሰዋል። በዓባይ ተፋሰስ ሀገራት መካከልም ሳይንሳዊ፣ ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ ሃብት አጠቃቀም የትብብር ምኅዳርን የሚያጎለብት ጥናቶችን ማካሄድ እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። የዓባይ ወንዝ የትብብር የወደፊት አቅጣጫ የውሃ መጠንን ከመከፋፈል ባሻገር የወንዙ ሥርዓት የሚፈጥራቸውን ጥቅሞች በፍትሐዊነትና በመጋራት ላይ መመሥረት እንዳለበት አመላክተዋል።
ነገን ተልሞ ለትውልድ መቅረጽ የመደመር መንግሥት መገለጫው ሆኗል።
Sep 5, 2026 543
የመደመር መንግሥት ለትውልድ የሚሻገር አገራዊ ወረት እያኖረ፤ በተጨባጭ ውጤቶችም እየተገለጸ ቀጥሏል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከባንዳ እስከ ባዳ በቅንጅት የተወረወሩበትን እያንዳንዷን ጠጠር በጥበብና በጽናት እየለቀመ የአገር ግንባታ ጡብ አድርጓቸዋል፤ ከጸኑ ፈተናዎች የሰሉ ዕድሎች ተፈልቅቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ “ኢትዮጵያዊ ጽናት እና አርቆ አስተዋይነት የታየበት” ሲሉ ያረጋገጡት እና መንግሥት ይፋ ያደረጋቸው የጉባ ብስራቶች የሀገራችን እምቅ አቅም በተግባር የሚገለጥባቸው ግዙፍ ማሳያዎች ናቸው። ከ30 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚፈጀው ይህ ማዕቀፍ የኢትዮጵያን የነገ ዕጣ ፈንታ በሰፊው የሚቀይር ታሪካዊ የጋራ ስኬት ነው። ለመደመር መንግሥት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የብልጽግናው ዋና መለኪያ ነው። የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ መጀመሩ የአርሶ አደራችንን ምርታማነት በብዙ እጥፍ ያሳድጋል። እንደ ሀገርም በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላርን እናተርፍበታለን።   በአፍሪካ ግዙፉ የሆነው አዲሱ የቢሾፍቱ አየር ማረፊያ ግንባታም እውን እየሆነ ነው። ይህ ፕሮጀክት ኢትዮጵያን የአህጉሪቱ ዋንኛ የሎጂስቲክስ፣ የንግድ እና የዲፕሎማሲ መገናኛ በማድረግ የጂኦ-ኢኮኖሚ አቅማችንን ወደ ታላቅ ከፍታ ያሸጋግረዋል። ብዙዎች በሀገራቸው እውን እንዲሆን የሚመኙትን ይህን ታላቅ ፕሮጀክት ኢትዮጵያውያን በጽናት ጀምረነዋል፤ እንፈጽመዋለን። የመደመር መንግሥት የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የነገው ትውልድ ዕድል የሚቀየር ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን በአጽኖት ተልሟል። የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ያለ ኢነርጂ ሉዓላዊነት የሚታሰብ አይደለም። ለዚህም ነው መንግሥት የኢነርጂ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የኢኮኖሚ ነጻነታችን ማዕዘን ድንጋይ ነው በሚል ስትራቴጂያዊ ትኩረት የሰጠው። ከታላቁ የህዳሴ ግድባችን ቀጥሎ የኢትዮጵያ ማንሰራራት ምልክት የሆነው የመጀመሪያው የጋዝ ፋብሪካችን ተመርቋል፤ ሁለተኛውም እየተገነባ ነው። የነዚህና ሌሎች በሂደት ላይ ያሉ ግዙፍ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ እና ሥራ መጀመር ከውጭ የሚገባውን የኢነርጂ ፍላጎት በማሟላት ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል፤ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ ማበብም ጽኑ መሠረት ይጥላል።   የልማት እውነተኛ ልክ የዜጎች ክብርና ማኅበራዊ ፍትህ መረጋገጥ ነው። መንግሥት ለዚህ አብላጫ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል። በመላው ሀገሪቱ የሚከናወነው የ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጀምሯል። ፕሮጀክቱ ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሚሊዮኖችን የቤት ባለቤት ያደርጋል። የከተሞችን ገጽታ በመቀየር ማኅበራዊ ፍትህን ያረጋግጣል። መደመር ማለት አብሮ ማደግ እና ሀብትን መጋራት ማለት ነው። እነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለሚሊዮን ወጣቶች ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራሉ። በዚህ ረገድ ገና ከጅምሩ ውጤቶች መመዝገብ ጀምረዋል። የመደመር መንግሥት ለትውልድ የሚያሻግረው ዕዳን ሳይሆን ምንዳን ነው። አዲሱን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፤ ነገን ዛሬ ተልሞ ለትውልድ መቅረጽ የመደመር መንግሥት ልዩ መገለጫ ሆኗል። ወገባችንን አስረን፣ መቀነታችንን አጥብቀን በላባችን ወዝ የምናኖራቸው ወረቶች ለነገው ትውልድ የሚቀሩ የብልጽግና ውርስ ይሆናሉ። በላባችን ጥረት ኢትዮጵያን በጸና መሠረት ላይ እናቆማለን። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ፖለቲካ
ከሀገራዊ ምክክሩ የተገኙ ምክረ-ሃሳቦች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባሉ
Sep 7, 2026 138
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ ከሀገራዊ ምክክሩ የተገኙ ምክረ-ሃሳቦች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርቡ ምክር ቤቱ ገልጿል። ከሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የተገኙ ምክረ- ሃሳቦች በየፈርጁ እየተደራጁ መሆኑንና በቀጣይ ምክረ-ሃሳቦቹን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ የኮሚሽኑ መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦ ኮሚሽኑ ከሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የተገኙ ምክረ-ሃሳቦችን በየፈርጁ በማደራጀት ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 01 ቀን - ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን ሲያስተባብር መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ኮሚሽኑ በርካታ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ምክረ-ሃሳቦች ማሰባሰብ የቻለ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያዊያን በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ለመመካከር ያሳዩት ቁርጠኝነት ውጤት ነው፡፡ ኮሚሽኑ በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 አንቀፅ 9 (10፣ 11፣ 12) በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ አጀንዳዎችን፣ የምክክሮቹን ሂደት፣ በምክክሮቹ የተገኙ ምክረ-ሃሳቦችን እንዲሁም ምክረ- ሃሳቦቹ በተግባር ላይ ሊውሉ የሚችሉበትን ሥልት የሚገልጽ ሰነድ በማዘጋጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለአስፈጻሚ አካሉ እና ለሌሎች የሚመለከታቸዉ የመንግስት አካላት አቅርቦ፤ ለሕዝብም ይፋ እንደሚያደርግ፤ መንግሥት ከሀገራዊ ውይይቶች የሚገኙ ምክረ-ሃሳቦችን በተግባር ላይ ለማዋል እንዲችል ግልፅ እና ተጨባጭ የሆነ ዕቅድ እንዲዘጋጅ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ፤ እንዲሁም የምክረ-ሃሳቦቹን አፈፃፀም መከታተል የሚያስችል ሥርዓት እንደሚዘረጋ በአዋጁ ተደንግጓል፡፡ ይህንን መነሻ በማድረግ ኮሚሽኑ፦ በአሁኑ ሰዓት ከሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የተገኙ ምክረ-ሃሳቦችን በየፈርጁ በማደራጀት ላይ ይገኛል፤ በቀጣይ ምክረ-ሃሳቦቹን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል፤ በመቀጠልም ምክረ-ሃሳቦቹን አግባብነት ባለው መንገድ ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል፤ በመጨረሻም ምክረ-ሃሳቦቹን ለአስፈፃሚ በማቅረብ ተፈፃሚነታቸውን ይከታተላል፡፡
የመንግሥት አዳዲስ እሳቤዎች በተለያዩ መስኮች የሚጨበጡ እመርታዎች እንዲመዘገቡ አድርገዋል - የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Sep 6, 2026 412
አዳማ ፤ ጳጉሜን 01/2018 (ኢዜአ) ፦ ያለፉት ዓመታት በመንግሥት አዳዲስ እሳቤዎችና በህዝቡ ትብብር በተለያዩ መስኮች የሚታዩና የሚጨበጡ እመርታዎች መመዝገባቸውን የተለያዩ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ወደ አዲስ ዓመት በሚደረገው ሽግግር የጳጉሜን 1 'የእመርታ ቀን' አስመልክተው ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ምክትል ሰብሳቢ አቶ በየነ ደሳለኝ፤ የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች መከበራቸው ሀገሪቱ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች በማንሳት ቀጣይ ስንቅ ለማድረግ የሚያነሳሳ ይሆናል ብለዋል። መንግሥት ባለፉት ዓመታት በሀገር በቀል እሳቤዎችና ፖሊሲዎች ሀገራዊ አቅሞችን መጠቀም ያስቻሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችንና በርካታ የልማት ኢንሼቲቮችን በመተግበር አስደናቂ እመርታዎች ማስመዝገቡን አንስተዋል። በተለይም በግብርናው ዘርፍ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ላይ የመጣው ለውጥ እና የታየው ስኬት ሊደነቅ የሚገባው ነው ብለዋል። የተለያዩ የግብርና ኢንሼቲቮች የተረጂነትና የጠባቂነት አስተሳሰብን በማስወገድ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆኑንም አንስተዋል። በሌሎችም ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችም እመርታ የተመዘገበባቸውና አመርቂ ውጤት የተገኘባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በድምሩ ባለፉት ዓመታት በመንግሥት አዳዲስ እሳቤዎችና በህዝቡ ትብብር በተለያዩ መስኮች የሚታዩና የሚጨበጡ እመርታዎች የተመዘገቡበት መሆኑን ተናግረዋል። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ሥራ አስፈጻሚ እና የኦሮሚያ ክልል አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ ተሰማ፤ በመንግሥት ሀገር በቀልና አዳዲስ እሳቤዎች በመታገዝ ባለፉት ጥቂት አመታት አስደናቂ ውጤት መመዝገቡን ተመልክተናል ብለዋል። የውጭ ምንዛሪ እጥረትንና የዋጋ ግሽበትን በመቋቋም ጭምር የሀገሪቱን ገጽታ የቀየሩ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን በጥራት እና በፍጥነት በመፈጸም የላቀ እመርታ መታየቱንም አንስተዋል። በጥናት ላይ ተመስርቶ በሀገሪቱ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ መደረጉ ለዜጎች ሰፊ የስራ እድልን ከመፍጠር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ወጪን በመቀነስ ረገድ ትርጉም ያለው ስራ ተሰርቷል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የምሥራቅ ሸዋ ዞን አስተባባሪ ወይዘሮ ሠናይት በላይ፤ በአዲሱ ዓመት መባቻ ላይ የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች መከበራቸው በጎ ሀሳቦችን እንድናፈልቅ ልዩ ስሜት እንዲፈጠርብን ያደርጋል ብለዋል። መንግሥት በጥቂት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር በተለይም በመስኖ ስንዴን በማልማት ከሀገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሉ ትልቅ እመርታ መሆኑን ገልጸዋል። በቱሪዝም፣ ዲጂታላይዜሽን፣ የአረንጓዴ አሻራ ልማት፣ በአትክልትና ፍሬፍሬ ልማት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች እመርታ መመዝገቡን ማየት ችለናል ብለዋል።
የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Sep 6, 2026 429
አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 1 /2018 (ኢዜአ)፦የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእመርታ ቀንን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት፣አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል ብለዋል። ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል ነው ያሉት። በ "ሌማት ትሩፋት" የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን በማለት ገልፀዋል። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች መሆናቸውን ጠቁመዋል። ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው ብለዋል። #EthiopiaDelivers
ኢጋድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባውን ሊያደርግ ነው
Sep 6, 2026 436
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት 74ኛው አስቸኳይ ስብሰባውን መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም በጅቡቲ ያካሂዳል። በስብሰባው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች ይሳተፋሉ። በቀጣናው ሰላም እና ጸጥታ እንዲሁም በሌሎች አበይት ጉዳዮች ላይ ምክክር ይደረጋል። ይህ ስብሰባ አባል ሀገራት በቀጣናው ያለውን የጸጥታና የደህንነት ሁኔታ እና እየተከናወኑ ያሉ ቀጣናዊ ጥረቶችን በመገምገም ለሰላም፣ መረጋጋትና ትብብር ያላቸውን የጋራ አቋም እንዲያጠናክሩ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ የድርጅቱን ተልዕኮ እና በቀጣናው ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ላይ የሚያደርገውን ድጋፍ እና የኢጋድ ስምምነትን (IGAD Treaty) ተፈጻሚነት ማጠናከርን ጨምሮ በዋና ዋና ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል። ስብሰባው የኢጋድ አባል ሀገራት በቀጣናው የሚገኙ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመቅረፍ እንዲሁም ለሕዝቦቻቸው ሰላም፣ መረጋጋትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡበት እንደሆነም ተገልጿል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከኢጋድ ቁልፍ የፖሊሲ አደረጃጀቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ የድርጅቱን ሥራዎች በመምራትና በአባል ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና የሚጫወት ነው።
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!
Sep 6, 2026 432
እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል፤ በዚያ አግባብ የሚመጣ መሻሻል ከታለመዉ ግብ ለመድረስ የትውልዶችን ጥረት የሚጠይቅ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ግን በቁጭት ለዘመናት ከቆየንበት ኋላ ቀርነት እና ድህነት በአዝጋሚ ጉዞ ለመላቀቅ ስለማይቻል እመርታዊ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርገን ሠርተን ስኬቶችን እያስመዘገብን ነው፡፡ ያለፉት ጥቂት ዓመታት ጥረቶቻችን ውጤቶች የሚያሳዩትም ይህንኑ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ጀርባ ያጎበጡ የውጭ ዕዳዎችን ጫና በመቀነስ፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፣ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅም በማሻሻል፣ የማዕድን ሀብቶች አጠቃቀምን በማላቅ እመርታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡ የመንግሥት አጠቃላይ የማድረግ ዐቅም በእጅጉ ተለውጧል፡፡ ይህንን እመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ የተቻለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በማድረግ፤ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል፤ የዜጎችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በማሳደግ፤ የቢዝነስ ሥርዐቱን ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ፤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ዐቅም ከዜጋ ተኮር እና ብሔራዊ ጥቅም አንጻር በመግራት የመደመር መንግሥት ባደረገዉ ሰፊ ጥረት ነው፡፡ ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ የኃላፊነት ስሜት በሕጋዊ አግባብ መጠቀም ጀምራለች፤ ታዳሽ ኃይልን በማምረት ከራስ አልፎ ለቀጠናዉ የኃይል ምንጭ ኾናለች፤ ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በመተግበር ኹለንተናዊ ዕድገቶችን እያስመዘገበች መጥታለች፤ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በዓለም ገበያ ተወዳድራ የመሸጥ ዐቅም ፈጥራለች፡፡ የመንግሥት የልማት ዕቅድ ከቁጥ ቁጥ ወጥቶ ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ግብ አስቀምጦ እየተተገበረ ነው፡፡ በ2018 ዓ/ም በሁሉም መስክ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ለውጥ የመሸጋገር ሀገራዊ ራዕይን ማሳካት ተችሏል፡፡ ኢትዮጵያን በ2023 ዓ.ም አፍሪካዊት የብለጽግና ተምሳሌት የማድረግ ግብ ተቀምጦ ርብርብ እየተደረገ የስኬቱ ዋዜማ እየተቃረበ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመደመር መንግሥት በተነደፉ የፖሊሲ ሐሳቦች ኹለንተናዊ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዞን ጀምራለች፡፡ በገቢ አሰባሰብ ላይ የታየዉ እመርታ አንዱ አብነት ነው፡፡ የግብር እና ታክስ መሠረትን በማስፋት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፤ የግብር ከፋዩን የመንግሥት አገልግሎት እርካታ በመሶብ አንድ ማእከል እና በዲጂታል አገልግሎቶች ከፍ በማድረግ የላቀ አፈጻጸም ማሳየት ተችሏል፡፡ በዚህም የበጀት ጉድለትን በእጅጉ ማጥበብ ተችሏል፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የመንግሥት ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ዐቅም በእጅጉ አድጓል፡፡ ፕሮጀክቶች መቼ እንደሚጀመሩ እና በምን ያህል በጀት እንደሚፈጸሙ ብቻ ሳይኾን መቼ ተጠናቅቀው በትክክል አገልግሎት እንደሚሰጡ ጭምር በከፍተኛ የራስ መተማመን የመሠረት ድንጋይ ሲቀመጥ መናገር የሚቻልበት ቁመና ላይ ተደርሷል፡፡ እመርታዊ ስኬቶችን ዕውቅና ለመስጠት፣ በቀጣዮቹም ዓመታት የበለጠ እመርታዊ ስኬቶችን ለማስመዝገብ መዘጋጀት አስፈላጊ በመኾኑ ዛሬ ጳጒሜን 01 ቀንን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት!” በሚል መሪ መልእክት እያከበርን ነው፡፡ እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን! ጳጒሜን 01 ቀን 2018 ዓ.ም የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ በዓባይ ውሃ አጠቃቀም ላጣቻቸው የልማት ዕድሎችና ለደረሰባት ታሪካዊ በደል ማካካሻ የመጠየቅ ሕጋዊና ተፈጥሯዊ መብት አላት
Sep 5, 2026 659
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 30/2018 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ውሃ አጠቃቀም ላጣቻቸው ሰፊ የልማት ዕድሎች፣ ለደረሰባት ታሪካዊ በደልና ለተፈጸመባት ኢ-ፍትሐዊ ግፍ ተገቢውን ማካካሻ የመጠየቅ ሕጋዊ፣ ተፈጥሯዊና ኢኮኖሚያዊ መብት እንዳላት የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች የቀድሞ ሚኒስትር ዴኤታ ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር) ገለጹ። ብርሀኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር) የምስራቅ አፍሪካ ፖሊሲ ምርምር ኢንስቲትዩት መስራችና የቀድሞው ምክትል ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች የቀድሞ ሚኒስትር ዴኤታ ናቸው። ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ለዓባይ ወንዝ ከምታመነጨው ከፍተኛ የውሃ ድርሻ አኳያ ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ ሃብት አጠቃቀም እንዲሰፍን ስትታገል ቆይታለች። ኢትዮጵያ ለዓባይ ወንዝ የምታበረክተው ከፍተኛ የውሃ ድርሻና በታሪክ በነበራት ዝቅተኛ የውሃ አጠቃቀም መካከል ያለው አለመጣጣምና ልዩነት የፍትሐዊ ተጠቃሚነት መሰረታዊ ጥያቄን የሚያስነሳ ነው ብለዋል። በዓባይ ወንዝ ላይ ለዘመናት የቆየው ኢ-ፍትሐዊ የውሃ ሃብት አጠቃቀም ውስንነትም የታሪክ እርማትና ካሳም ጭምር የሚያስፈልገው ሕጋዊና ፍትሐዊ መሰረት ያለው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ከ86 በመቶ በላይ የዓባይ ውሃ ምንጭ ኢትዮጵያ ሆና ሳለ ምንም ሳትጠቀም፣ ግብፅ በአንጻሩ 85 በመቶ የወንዙን የውሃ ሃብት ስትጠቀም ቆይታለች ብለዋል። በዚህ መነሻነትም ኢትዮጵያ እስካሁን ለደረሰባት ታሪካዊና ኢ-ፍትሐዊ ኪሳራ ግልፅ ማካካሻ የመጠየቅ ሕጋዊና ፍትሐዊ መብት እንዳላት አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ በዓባይ ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባታል ያሉት ብርሃኑ (ዶ/ር)፤ የሥነ-ምኅዳር ሚዛን ለመጠበቅ ለምታበረክተው የልማት አስተዋጽኦ ካሳ ያስፈልጋታል ብለዋል። በቀጣይም ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ሕጋዊ ካሳ በአረንጓዴ ዐሻራና ሥነ-ምኅዳር ጥበቃ፣ የደን ልማትና ለታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት በምታበረክተው አስተዋጽኦ ልክ መታየት እንደሚኖርበት አብራርተዋል። የታችኛው የተፋሰሱ ሀገራትም ወንዙን ለመጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርጋቸውን ሁለንተናዊ የአረንጓዴ ልማት የመደገፍ ግዴታ ጭምር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ዓባይን ባለመጠቀሟ ብዙ የልማት ዕድል አምልጧታል ያሉት ብርሃኑ (ዶ/ር)፤ ይህም ሳይበቃ ግብፅ ወንዙን በብቸኝነት ከመጠቀም ባሻገር የኢትዮጵያ የግጭቶች ምንጭ ሆና ዘልቃለች ብለዋል። ግብፅ በጫካ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂና የሽብር ኃይሎችን በቁሳቁስ በመደገፍ ኢትዮጵያ በውክልና ጦርነት እንድትቆይ በማድረግ የባሕር መግቢያና መውጫ በሯን ጭምር እንዳሳጣቻት አስታውሰዋል። በዓባይ ተፋሰስ ሀገራት መካከልም ሳይንሳዊ፣ ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ ሃብት አጠቃቀም የትብብር ምኅዳርን የሚያጎለብት ጥናቶችን ማካሄድ እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። የዓባይ ወንዝ የትብብር የወደፊት አቅጣጫ የውሃ መጠንን ከመከፋፈል ባሻገር የወንዙ ሥርዓት የሚፈጥራቸውን ጥቅሞች በፍትሐዊነትና በመጋራት ላይ መመሥረት እንዳለበት አመላክተዋል።
ነገን ተልሞ ለትውልድ መቅረጽ የመደመር መንግሥት መገለጫው ሆኗል።
Sep 5, 2026 543
የመደመር መንግሥት ለትውልድ የሚሻገር አገራዊ ወረት እያኖረ፤ በተጨባጭ ውጤቶችም እየተገለጸ ቀጥሏል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከባንዳ እስከ ባዳ በቅንጅት የተወረወሩበትን እያንዳንዷን ጠጠር በጥበብና በጽናት እየለቀመ የአገር ግንባታ ጡብ አድርጓቸዋል፤ ከጸኑ ፈተናዎች የሰሉ ዕድሎች ተፈልቅቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ “ኢትዮጵያዊ ጽናት እና አርቆ አስተዋይነት የታየበት” ሲሉ ያረጋገጡት እና መንግሥት ይፋ ያደረጋቸው የጉባ ብስራቶች የሀገራችን እምቅ አቅም በተግባር የሚገለጥባቸው ግዙፍ ማሳያዎች ናቸው። ከ30 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚፈጀው ይህ ማዕቀፍ የኢትዮጵያን የነገ ዕጣ ፈንታ በሰፊው የሚቀይር ታሪካዊ የጋራ ስኬት ነው። ለመደመር መንግሥት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የብልጽግናው ዋና መለኪያ ነው። የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ መጀመሩ የአርሶ አደራችንን ምርታማነት በብዙ እጥፍ ያሳድጋል። እንደ ሀገርም በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላርን እናተርፍበታለን።   በአፍሪካ ግዙፉ የሆነው አዲሱ የቢሾፍቱ አየር ማረፊያ ግንባታም እውን እየሆነ ነው። ይህ ፕሮጀክት ኢትዮጵያን የአህጉሪቱ ዋንኛ የሎጂስቲክስ፣ የንግድ እና የዲፕሎማሲ መገናኛ በማድረግ የጂኦ-ኢኮኖሚ አቅማችንን ወደ ታላቅ ከፍታ ያሸጋግረዋል። ብዙዎች በሀገራቸው እውን እንዲሆን የሚመኙትን ይህን ታላቅ ፕሮጀክት ኢትዮጵያውያን በጽናት ጀምረነዋል፤ እንፈጽመዋለን። የመደመር መንግሥት የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የነገው ትውልድ ዕድል የሚቀየር ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን በአጽኖት ተልሟል። የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ያለ ኢነርጂ ሉዓላዊነት የሚታሰብ አይደለም። ለዚህም ነው መንግሥት የኢነርጂ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የኢኮኖሚ ነጻነታችን ማዕዘን ድንጋይ ነው በሚል ስትራቴጂያዊ ትኩረት የሰጠው። ከታላቁ የህዳሴ ግድባችን ቀጥሎ የኢትዮጵያ ማንሰራራት ምልክት የሆነው የመጀመሪያው የጋዝ ፋብሪካችን ተመርቋል፤ ሁለተኛውም እየተገነባ ነው። የነዚህና ሌሎች በሂደት ላይ ያሉ ግዙፍ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ እና ሥራ መጀመር ከውጭ የሚገባውን የኢነርጂ ፍላጎት በማሟላት ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል፤ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ ማበብም ጽኑ መሠረት ይጥላል።   የልማት እውነተኛ ልክ የዜጎች ክብርና ማኅበራዊ ፍትህ መረጋገጥ ነው። መንግሥት ለዚህ አብላጫ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል። በመላው ሀገሪቱ የሚከናወነው የ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጀምሯል። ፕሮጀክቱ ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሚሊዮኖችን የቤት ባለቤት ያደርጋል። የከተሞችን ገጽታ በመቀየር ማኅበራዊ ፍትህን ያረጋግጣል። መደመር ማለት አብሮ ማደግ እና ሀብትን መጋራት ማለት ነው። እነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለሚሊዮን ወጣቶች ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራሉ። በዚህ ረገድ ገና ከጅምሩ ውጤቶች መመዝገብ ጀምረዋል። የመደመር መንግሥት ለትውልድ የሚያሻግረው ዕዳን ሳይሆን ምንዳን ነው። አዲሱን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፤ ነገን ዛሬ ተልሞ ለትውልድ መቅረጽ የመደመር መንግሥት ልዩ መገለጫ ሆኗል። ወገባችንን አስረን፣ መቀነታችንን አጥብቀን በላባችን ወዝ የምናኖራቸው ወረቶች ለነገው ትውልድ የሚቀሩ የብልጽግና ውርስ ይሆናሉ። በላባችን ጥረት ኢትዮጵያን በጸና መሠረት ላይ እናቆማለን። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ማህበራዊ
የአርቲስት እልፍነሽ ቀኖ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ነገ በአምቦ ይፈጸማል
Sep 7, 2026 52
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ የአንጋፋዋ አርቲስትና የሰብአዊ መብት ተሟጋች እልፍነሽ ቀኖ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ነገ ጳጉሜን 03 ቀን 2018 ዓ.ም በክብር ሥነ-ሥርዓት ይፈጸማል።   አዘጋጅ ኮሚቴው በሰጠው መግለጫ መሠረት፤ የአርቲስቷ አስከሬን ሽኝት ነገ ከጠዋቱ 11:00 እስከ 12:00 ከኮሪያ ሆስፒታል ወደ መኖሪያ ቤቷ የሚደረግ መሆኑን ገልጿል። ከጠዋቱ 12:00 እስከ 1:00 ባለው ጊዜ ደግሞ አስክሬን ከመኖሪያ ቤቷ ወደ አዲስ አበባ ስታዲየም ይወሰዳል። የአርቲስቷ ወደጆች ጓደኞችና አድናቂዎችም ነገ ከጠዋቱ 1:00 እስከ 3:00 በአዲስ አበባ ስታዲየም ተገኝተው አሸኛኘት ካደረጉላት በኋላ ወደ አምቦ ሽኝት እንደሚደረግ አዘጋጅ ኮሚቴው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ገልጿል።   የዕድሜ ልክ ትግሏን ለሰው ልጆች ነፃነትና ለህዝብ ድምፅነት የሰጠችው አርቲስት እልፍነሽ ቀኖ፣ በህይወት እያለች "ከዚህ ዓለም ስሰናበት ቀብሬ አምቦ ይሁን" ባለችው ኑዛዜ መሠረት፣ አስተባባሪ ኮሚቴው የጀግናዋን ፍላጎት በማክበር የመጨረሻ እረፍቷ በአምቦ ከተማ እንዲሆን መወሰኑ ተመላክቷል። በዜማዎቿ የሕዝብን ብሶትና ተስፋ ስታንጸባርቅ የኖረችው ይህች ታላቅ አርቲስት፣ በግል ሕይወቷም የሁለት ሴቶችና የአንድ ወንድ ልጅ እናት በመሆን መልካም ቤተሰብን ያፈራች እናት ነበረች።
የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ነው
Sep 7, 2026 170
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ የከንቲባ ጽህፈት ቤት ገለጸ። የአዲስ አመት መቀበያ የሆነችው ጳጉሜን ቀናት በተለያየ ስያሜዎች እየተከበሩ ሲሆን የዛሬው ጳጉሜን 2 ደግሞ በማንሰራራት ተሰይሟል። የአዲስ አበባ የማንሰራራት ማሳያ የሆነው የትራንስፖርት ዘርፍም ለከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ቀኑን እያከበረ መሆኑም ተገልጿል። ለግማሽ ቀን በሚቆየው ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የከተማ አውቶብስና የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ለደንበኞቻቸው መልካም የአዲስ አመት በመመኘት ጭምር እየተሳተፉ መሆናቸውም እንዲሁ። በቦሌ ሚሊኒየም አካባቢ የተሰጠውን ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው እንዳሉት በነጻ ትራንስፖርቱ 1 ነጥብ 1 ሚሊየን የመዲናዋ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። የአዲስ አበባ የማንሰራራት ማሳያ ከሆኑ ልማቶች መካከልም የትራንስፖርት ዘርፉ ዋነኛው መሆኑን ጠቅሰው፤ የከተማዋን እድገት የሚመጠን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማስፋፋት ዘርፉ ማንሰራራት መቻሉን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ ከተማን የአፍሪካ የፅዳትና ውበት ተምሳሌት የሚያደርጉ እመርታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል
Sep 6, 2026 310
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ከተማን በአፍሪካ የፅዳትና ውበት ተምሳሌት የሚያደርጉ እመርታዊ ለውጦች መመዝገባቸውን የከተማዋ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሳዲቅ ሽኩር ገለፁ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን ገጽታ ለመቀየርና ጽዳቷን ለመጠበቅ ያለመ ከተማ አቀፍ የጽዳት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በልደታ ክፍለ ከተማ በይፋ አስጀምሯል። የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች፣ የጽዳት አምባሳደሮች፣ አርቲስቶች፣ በጎ ፈቃደኞችና የጸጥታ አካላት በከተማ አቀፍ የጽዳት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ተሳትፈዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሳዲቅ ሽኩር እንዳሉት፣ አዲስ አበባን ውብና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ ሁሉንም ሕብረተሰብ ክፍል ያሳተፈ ንቅናቄ መፍጠር ያስፈልጋል። ጷጉሜን 1 "የእምርታ ቀን" የከተማዋን የጽዳትና ውበት ስኬቶች በማስቀጠል የጽዳትን ባህል ለማዳበር ራሳችንን የምናድስበት ነው ብለዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የከተማዋን ገጽታ ለማሻሻል፣ የኢኮኖሚ እድገትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል። ከተማዋ "ለአፍሪካ መዲናነት አትመጥንም" ከሚል ስም ተላቃ፣ ዛሬ ላይ በአፍሪካ የጽዳትና ውበት ተምሳሌት ለመሆን መብቃቷ እንደ ትልቅ እመርታ እና ስኬት የሚታወስበት ቀን መሆኑን ገልጸዋል። የጽዳትና ውበት ሥራዎችን በመንግሥት ደረጃ ብቻ ማስቀጠል ስለማይቻል ሕብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት በቀጥታ ባለቤት እንዲሆኑም አሳስበዋል። ይህ ከተማ አቀፍ የጽዳት ንቅናቄ በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች በተቀናጀ መልኩ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ ሕብረተሰቡም መኖሪያና ሥራ አካባቢውን በመጠበቅ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አምባሳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ የምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን ፀሃይ በበኩሉ፤ አዲሱን ዓመት አካባቢን በጽዳት እንቅስቃሴዎች መጀመር የሚያበረታታ እና በጎ ምልከታን የሚፈጥር ተግባር ነው ብለዋል። ዘላቂ የሆነ የጽዳት እንቅስቃሴ ለማድረግ ማህበረሰቡን እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ንቅናቄ መፍጠሩ፣ የህብረት እና የጥንካሬ ማሳያ እንደሆነ ገልጸዋል። የጽዳት አምባሳደር አርቲስት ሙሉነህ ዘለቀ በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት በህዝብና በመንግሥት ቅንጅት ከተማዋን በመለወጥ ረገድ ከፍተኛ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል። ይህ ለውጥ በአዲስ አበባ ብቻ ሳይወሰን በሌሎች የሀገሪቷ ክልሎችና ከተሞችም እየተስፋፋ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የጽዳት አምባሳደር አርቲስት ኤልያስ ተባባል በሰጡት አስተያየት፣ አዲስ አበባ የአፍሪካ ዋና ከተማ በመሆኗ ሁልጊዜ ጽዱ እና ንጹህ መሆን አለባት ብለዋል። የጽዳት አምባሳደር ኮሜዲያን ማርቆስ ፍቅሩ፣ የጽዳት ሥራ የአንድ ወቅት እንቅስቃሴ ሳይሆን ሁልጊዜ በየቀኑ በየአካባቢው ሊከናወን የሚገባ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። በጽዳት ዘመቻው በመሳተፏ የተሰማትን ደስታ የገለጸች ሰርካለም ተፈራ እንደተናገረችው፤ የጽዳት እንቅስቃሴው ለከተማዋ ነዋሪዎች በርካታ ጥቅሞች አሉት።        
ኢትዮ ቴሌኮም በአፋር ክልል ለትምህርት ሥራ ስኬታማነት የበኩሉን እየተወጣ ነው
Sep 6, 2026 147
ሰመራ፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮ-ቴሌኮም በአፋር ክልል ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ ለትምህርት ሥራ ስኬታማነት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ። ኢትዮ ቴሌኮም በሠመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር አሰቦዳ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች ዛሬ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል። በርክክቡ መርሃ ግብሩ ላይ የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ ኀላፊ ሙሳ አደም እንዳሉት ኢትዮ ቴሌኮም ለተማሪዎች ያደረገው ድጋፍ በክልሉ የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት ተደማሪ አቅም አለው።   ዛሬ የተደረገው የመማሪያ ቁሳቅስ ድጋፍ ከ4 ሺህ በላይ ተማሪዎችን የትምህርት ቁሳቁስ ፍላጎት በመሸፈን ለትምህርት ስራ ስኬታማነት አዎንታዊ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። በኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ምስራቅ ሪጅን ዋና ዳይሬክተር አቶ ብርሃነ ፍፁም ኢትዮ ቴሌኮም ከመደበኛ ስራው በተጓዳኝ ማህበራዊ ሃላፊነቱን በመወጣት ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የትምህርት ግብአትን ማቅረቡን ተናግረዋል። ድጋፉ ለትምህርት ሥራ ስኬታማነት ጉልህ አስተዋጾ እንዳለው ገልጸው፣ ለድጋፉ ከ2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉንና በቀጣይም ተመሳሳይ ተግባራት እንደሚጠናከሩ ተናግረዋል። የአሰቦዳ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር መሀመድ ገዶ በበኩላቸው፣ በትምህርቱ ቤቱ ድጋፍ ለሚያሻቸው ተማሪዎች የተደረገው ድጋፍ የወላጆችን ችግር የሚያቃልል መሆኑን ተናግረዋል። በዛሬው ዕለት የተደረገላቸው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በትምህርታቸው ጠንክረው ለመማር ተነሳሽነት መፍጠሩን የገለፁት ደግሞ ተማሪ ፋጡማ መሐመድ እና ተማሪ መሐመድ አህመድ ናቸው።  
ኢኮኖሚ
ማዕከሉ እንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በስፋት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ ነው
Sep 7, 2026 38
አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 2/2018(ኢዜአ)፦መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በስፋት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል ገለጸ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ሥር የሚገኘው የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል፣ መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረበ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አሌክስ ደመቀ እንደገለጹት፤ ማዕከሉ አርሶ አደሮችን ለማቋቋም፣ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ገበያ ለማረጋጋት ነው የተቋቋመው፡፡ በአሁኑ ወቅት የደለቡ በሬዎችንና የእንስሳት ተዋጽኦዎችን በማዕከሉ እና በተለያዩ ቦታዎች በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ነው የገለጹት፡፡ በዓሉን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጁ ባዛሮች ላይም ከ350 ሺህ በላይ እንቁላል ማቅረቡን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ በማዕከሉ የተሰማሩ አምራቾች በበኩላቸው መንግሥት ባመቻቸላቸው ዕድል ተጠቅመው ምርቶቻቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።   የእንቁላል አምራች አበራሽ ንጉሤ እንዳሉትም ምርታቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። የወተት ተዋጽኦ አምራቿ ወይዘሮ የሺወርቅ ዳኛቸው ለበዓሉ የሚሆኑ እንደ ቅቤና አይብ ያሉ ምርቶችን ከውጭው ገበያ በቅናሽ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።   ማዕከሉ ከተቋቋመበት ከ2015 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ በእንቁላል ጣይ ዶሮ እርባታ፣ በእንስሳት ማድለብና በወተት ላም እርባታ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ ይገኛል።    
ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ማንሰራራት ሚናውን እያጎለበተ የሚገኘው - የማዕድን ዘርፍ
Sep 7, 2026 90
አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 2/2018(ኢዜአ)፦መንግስት ለማዕድን ዘርፍ ልማት የሰጠው ልዩ ትኩረት እና እየተገኘ ያለው ውጤት ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገቱ ማንሰራራት የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ኢትዮጵያ በርካታ የማዕድን ሀብት ከሚገኝባቸው ሀገራት መካከል አንዷ ብትሆንም ቀደም ባሉት ጊዜያት ሀብቱን በማልማት ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ከማድረግ አንጻር አመርቂ አልነበረም። ባለፉት ዓመታት መንግሥት በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ ማዕድንን አንዱ መሠረታዊ የኢኮኖሚ ልማት ምሰሶ በማድረጉ ዘርፉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ምቹ ምህዳር ተፈጥሯል። የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ ብርሃኔ ያዴሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በመደመር መንግሥት በማዕድን ዘርፍ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች በኢንዱስትሪው እንዲሰማሩ የፖሊሲ እና ምቹ ምህዳር መፍጠር ተችሏል። የማዕድን ዘርፍ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለተኪ ምርት ዕድገት እና የውጭ ምንዛሬን ለማዳን በርካታ ፋይዳዎች እንዳለው አንስተው፤ ባለፉት አመታት ለዘርፉ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል። የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን በስፋት በዘርፉ ማሰማራት የሚያስችሉ አጋዥ የማዕድን ፖሊሲና ህግጋት ተሻሽለው ለማጸደቅ በሂደት ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ቀደም ሲል ማዕድናት በጥሬው ወደ ውጭ ይላኩ እንደነበር አንስተው በአሁኑ ወቅት እሴት ጨምሮ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ማቅረብ ላይ ትኩረት መደረጉንም ገልጸዋል። ለአብነትም በወርቅ፣ በድንጋይ ከሰል፣ ኦፓልና ሌሎች ጌጣጌጦች እሴት ተጨምሮባቸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡበት አሰራር በመፈጠሩ ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል። ባለፉት አራት ዓመታት በወርቅ ዘርፍ የውጭ ምንዛሬ ግኝት ላይ ከፍተኛ ስኬት መገኘቱን አንስተው፤ የወርቅ ማጣሪያ በሀገር ውስጥ እንዲገነባ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። የወርቅ ምርት በ2015 ዓ.ም ከነበረበት 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቶን በ2018 ዓ.ም ወደ 44 ሚሊዮን ቶን ማደጉንና የውጭ ምንዛሬ ግኝቱም ከ196 ሚሊዮን ዶላር ወደ 5 ነጥብ 7 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ማደጉን ተናግረዋል፡፡ በሲሚንቶ ምርትም እንዲሁ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቶን ወደ 10 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቶን በማደግ ከፍተኛ እመርታ ማሳየቱን ገልጸዋል። የድንጋይ ከሰል ምርት ቀደም ሲል በጥሬው ይቀርብ እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ እሴት ተጨምሮበት ወጥ በሆነ ጥራት ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች ግብዓት እስከ 75 በመቶ መሸፈን የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል ቀደም ሲል የሴራሚክ ምርት በአብዛኛው ከውጭ ይገባ እንደነበር አውስተው አሁን ላይ መንግስት ለዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ በሀገር ውስጥ የማምረት አቅም አድጓል ብለዋል። በዚህም በሴራሚክ ምርት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን መሸፈንና ለግዥ ይወጣ የነበረን የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ጨምረው ገልጸዋል።        
በግብርናው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለው ዕመርታዊ ለውጥ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ብስራት ነጋሪ ነው
Sep 7, 2026 67
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ በክልሎች ግብርናውን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሁለንተናዊ ዕድገት ለማምጣት የተጀመረው ጥረት የማንሰራራት ዘመን ብስራት ነጋሪ መሆኑን የተለያዩ ክልሎች የግብርና ቢሮ ኃላፊዎች ገለጹ። ኢትዮጵያ ግብርናውን በመካናይዜሽን፣ በኩታ ገጠም እርሻ፣ እንዲሁም ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ ግብዓቶችን በስፋት በማቅረብ በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ማሳደግ ችላለች። የአሰራር ሥርዓቶችን በማዘመንና እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓይነት ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ በመጠቀም እንደ ሀገር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ማሳካት የሚያስችል ውጤት ተመዝግቧል። ግብርናው ለኢኮኖሚያዊ ማንሰራራትና ለገጠር መዋቅራዊ ሽግግር ገንቢ ሚና መወጣት የሚችልበትን አቅም ፈጥሯል። በኢትዮጵያ ግብርናውን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሁለንተናዊ ዕድገት ለማምጣት የተጀመረው ጥረት የማንሰራራት ዘመን ብስራት ነጋሪ ነው። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር ለኢዜአ እንዳሉት፤ መሬት፣ ጊዜ፣ ጉልበት እና ሀሳብን አቀናጅቶ በመጠቀም በሰብል ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ መጥቷል። በዚህም በክልሉ በ2018 ወደ 1 ነጥብ 28 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በሰብል በመሸፈን፤ አጠቃላይ የሰብል ምርት መጠኑን ከ161 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማድረስ ተችሏል ብለዋል። ከዚህም ባለፈ የሰብል ብዝሃነትን በማስፋት ከውጭ የሚገባውን ምርት የሚተኩ፣ ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ማምረት መጀመራቸውን ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ማስረሻ በላቸው፤ በክልሉ "የማይታረስ መሬት ሊኖር አይገባም" በሚል በድግግሞሽ የሚታረሰውን መሬት ከ560 ሺህ ሄክታር ወደ 801 ሺህ ሄክታር በማሳደግ የኢትዮጵያን የማንሰራራት ዘመነ ለማብሰር መሰረት የሚጥሉ ውጤቶች መመዝገባቸው ገልጸዋል። በሆርቲካልቸር ልማት ከ41 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን በመግለጽ፤ ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለዓለም ገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ተገኝቷል ብለዋል። በሌማት ትሩፋት ሥራዎችን ለማጠናከር የመኖ ማሽኖች ተከላ፣ የዓሳ ዕርባታ ማዕከላት ግንባታ፣ የዶሮ ማቆያና መሰል ማስፋፊዎችን እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የምክትል ቢሮ ኃላፊ አጀበ ስንሻው በበኩላቸው፤ በክልሉ የግብርና ሜካናይዜሽን በማስፋት 1 ነጥብ 4 ሚሊዬን ሄክታር መሬት በትራክተር ይታረሳል ብለዋል። ለአርሶ አደሩ 7 ነጥብ 1 ሚሊዬን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እና ከ 310 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር በማቅረብ የአቅርቦትን ማሻሻልና የታቀደውን የግብርና ግብዓት ማሳካት መቻላቸውን ገልጸዋል። በኩታ ገጠም እርሻ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ፣ ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብ እና ለውጭ ገበያ የሚቀርበን ምርት ማሳደግ የሚያስችል ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።      
ኢትዮጵያ የንጹህ ኃይል ልማቷን አጠናክራ ትቀጥላለች - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
Sep 7, 2026 84
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የንጹህ ኃይል ልማቷን አጠናክራ በመቀጠል ለጎረቤት ሀገራት የምታቀርበውን የኃይል መጠን ለማሳደግ እየሰራች መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ዱባይ እየተካሄደ ባለው ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ጉባኤ (AIM Congress) ላይ ንግግር አድርገዋል።   ፕሬዝዳንት ታዬ ለታዳሚዎች ባስተላለፉት መልዕክት፤ ጉባኤው የዓለም ኢኮኖሚ መዋቅር በመሰረታዊነት እየተለወጠና የቴክኖሎጂ ለውጦች አጠቃላይ ሁኔታዎችን እየቀየረ ባለበት ጊዜ መካሄዱ ጠቃሚ ያደርገዋል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ተለዋዋጭ የጂኦ ፖለቲካ ሁኔታዎች የዓለምን የንግድ የእሴት ሰንሰለት እየወሰነ መምጣቱን ገልጸው፤ እነዚህ አዲስ ክስተቶች በማደግ ላይ ላሉ ሀገሮች በተለይም ለአፍሪካ ካመጡት ችግር ባልተናነሰ ወደ ውስጥ ለመመልከት ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል። ይህንንም ተከትሎ የአፍሪካ አገራት በአፍሪካ ኅብረት በኩል የዚህ ተለዋዋጭ ዓለም ክስተት ተመልካች ሳይሆኑ ዋነኛ ተሳታፊና ሥርዓት ገንቢ አካል ለመሆን የጋራ መግባባት መደረሱን ተናግረዋል። በተለይም ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት እየተገበረቻቸው ያሉትን ተከታታይ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራሞች ከዚህ አኳያ የተቃኙ መሆናቸውን አብራርተዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ እንደገለጹት፤ አፍሪካ ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚ እንድትገነባ ያላትን የስትራቴጂክ ኢንቨስትመንት ዕድሎች አሟጣ ለመጠቀም አምስት ዋና ዋና ጉዳዮችን ማከናወን ይጠበቅባታል። አንደኛ በአፍሪካ የጋራ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ለማምጣት በንጹህ የኤሌትሪክ ኃይል ማስፋፋት ላይ ትኩረት ሊያደርጉ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ ሀገሮች በተለይም ከንፋስ፣ ከፀሐይ፣ ከአንፋሎትና ከኃይድሮ ኤሌክትሪክ ልማት ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ኢትዮጵያም የንጹህ የኃይል አማራጭን እንደ ሀገራዊ ሃብት ብቻ ሳይሆን ለፈጣን የኢኮኖሚ እድገት መሰረት አድርጋ ትወስደዋለች ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ከንጹህ ሃይል ብቻ 60 ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌትሪክ ሃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት ገልጸው፤ እኤአ 2030 ኢትዮጵያ 13 ሺህ ሜጋ ዋት ለማመንጨት እቅድ እንዳላት ተናግረዋል። በዚህም ለምስራቅ አፍሪካና ለሌሎች አገሮች የሚቀርበውን የኃይል አቅርቦት ለማሳደግ እንደምትሰራም ጠቁመዋል። በሁለተኛ ደረጃ የአፍሪካ አገራት በግብርና ዘርፍ ላይ መሥራት እንዳለባቸው ተናግረው፤ ኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተለይም በስንዴ ምርት ዘርፍ ያስመዘገበችውን እመርታ በተሞክሮ ለታዳሚው አቅርበዋል።   በሦስተኛ ደረጃ የአፍሪካ አገሮች ከወርቅ ጀምሮ እስከ ኮባልትና ሊቲየም ድረስ ያላቸውን የተለያዩ የማዕድን ሀብቶች መጠቀም እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ታንታለም የተባለውን ማዕድን በማምረት በዓለም ስድስተኛ ደረጃ መያዟን ገልጸዋል። የአፍሪካ አገሮች ለዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት የመሰረተ ልማት ግንባታና የዲጂታል መሰረተ ልማት ማስፋፋት ላይ ትኩረት አድርገው መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚሰራውን ሥራ ለአብነት ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋነኛ የትስስር ማዕከልነቷን ለማፅናት የሚያስችላትን የቢሾፍቱ አየር መንገድ በ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር እየገነባች መሆኑን አስረድተዋል። በሌላ በኩል ሦስት ነጥብ አራት ትሪሊዮን ዶላር የሚጠጋ የአገራት አጠቃላይ አገራዊ ምርት የገበያ አቅም ያለው የአፍሪካ ነጸ የንግድ ቀጣና የመሰሉ ፕሮጀክቶች ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተናግረዋል። በአምስተኛ ደረጃ የአፍሪካ አገራት ያላቸውን የሰው ኃይል በአግባቡ ሊጠቀሙ እንደሚገባ አስገንዘበው፤ ኢትዮጵያ በተለይም በዲጂታል ቴክኖሎጂው ክህሎት ወጣቶች ያላቸውን አቅም ለማጎልበት የኮደር ሥልጠና እየሰጠች መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህ ኢኒሼቲቭ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰው፤ ለዚህም ምስጋና አቅርበዋል። የተለያዩ የአገራት መሪዎች፣ የኢንቨስትመንት ኩባንያዎች ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የምርምር ተቋማት ተወካዮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ዛሬ በዱባይ የተጀመረው ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክሮ ከነገ በስትያ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
መሶብ የአንድ ማዕከል፤ የመደመር መንግሥት የአገልግሎት ትራንስፎርሜሽን ማስፈንጠሪያ 
Sep 6, 2026 232
መሶብ የአንድ ማዕከል፤ የመደመር መንግሥት የአገልግሎት ትራንስፎርሜሽን ማስፈንጠሪያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት የተጀመረው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የዜጎችን እንግልት በመቀነስና የመንግሥት አሰራርን በማዘመን ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አሰራርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማዘመን፣ የወረቀት ስራንና እንግልትን በማስቀረት ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊና ግልጽ አገልግሎት ለመስጠት የተዘረጋ ስርዓት ነው። ፕሮጀክቱ አገልግሎት ፈላጊዎች በአንድ ማዕከል በርካታ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፤ ይህም ህብረተሰቡ የመሬት አስተዳደር፣ የኢንቨስትመንት፣ የገቢዎችና ሌሎችንም የመንግሥት አገልግሎቶች በኦንላይንና በአካል ማግኘት የሚያስችል ነው። አገልግሎቱ በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በባህር ዳር እና በሌሎችም የክልሎች ከተሞች ተግባራዊ መሆን የጀመረ ሲሆን፤ ማዕከላቱን በየደረጃው እስከ ወረዳ ድረስ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተንቀሳቃሽ መሶብ አገልግሎትን በአዲስ አበባ ባስጀመሩበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት የቆዩ የአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎችን በመፍታት የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውታል። ይህንን ለማሳካት በመንግሥት፣ በግል ኩባንያዎችና በእያንዳንዱ ዜጋ ዘንድ የባህልና የአስተሳሰብ ለውጥ መምጣት እንዳለበትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል። ሀገሪቷን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መንግሥት በትኩረት እየሰራባቸው ካሉ አምስት የኢኮኖሚ አምዶዎች መካከል ቴክኖሎጂ አንደኛው መሆኑን ነው በወቅቱ ያብራሩት። ቴክኖሎጂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የቱሪዝም ዘርፍን ለማዘመን እንዲሁም ዲጂታል የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ሁሉንም የልማት ዘርፎች የሚያቀናጅ ዋና መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል።   የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ሲሆን፤ በተለይም የአገልግሎት አሰጣጥን ወደ ዘመናዊና ዲጂታል ሥርዓት በመቀየር የዜጎችን እንግልት መቀነስ አስችሏል። የ“ዲጂታል 2030” ስትራቴጂ፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተገኙ ስኬቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሀገራዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግርም አብራርተዋል። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ በሀገሪቷ ባሉ ከ108 በላይ ማዕከላት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ተችሏል።   የአገልግሎቱ አጠቃላይ ሀገር አቀፍ የተገልጋዮች እርካታ መጠን ከ99 በመቶ በላይ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። በዘመናዊ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት መስጫዎች ማዕከላት በአካል መጥተው መገልገል ለማይችሉ ዜጎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንና ተደራሽነትን ይበልጥ ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አጽንኦት መስጠታቸው ይታወሳል። በመዲናዋ የተዘረጋው የዲጂታል መሶብ አገልግሎት፣ በከተማ ደረጃ እየተካሄደ ላለው የዲጂታል ሽግግር ማሳያ ከመሆኑም በላይ በነዋሪዎች ዘንድ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሠራርን በመቀነስ የተገልጋዮችን እርካታ ለማሳደግ አስችሏል - ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
Sep 5, 2026 220
ጎንደር፤ ነሐሴ 30/2018 (ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሠራርን በመቀነስ የተገልጋዮችን እርካታ ለማሳደግ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። ርዕሰ መሥተዳድሩ አረጋ ከበደ የጎንደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ዛሬ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። ርዕሰ መሥተዳድሩ በዚሁ ወቅት መሶብ የአንድ ማዕከል የመንግሥት የአገልግሎት አሠጣጥ ሪፎርም አካል በመሆን ዘልማዳዊ እና እንግልት የበዛበትን አሠራር እየቀየረ ነው ብለዋል። የመንግሥት ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት በአንድ ማዕከል በማሠባሠብ፣ በማደራጀት፣ ዲጂታል በማድረግ፣ ብልሹ አሠራርን በመቀነስ የተገልጋዮችን እርካታ ለማሻሻል እያገዘ መሆኑንም አስረድተዋል። በክልሉ ስድስት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን ተገልጋይን መሠረት ያደረገ በመሆኑ የነበረውን እንግልት የበዛበት አሠራር ሁለንተናዊ በሆነ መንገድ እየቀረ መሆኑን አንስተዋል። የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተሻለ ተደራሽነትን፣ የላቀ ቅልጥፍናን፣ ግልጽነትን እና ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥ መኾኑንም አንስተዋል። አገልግሎቱ የመንግሥት ተቋማትን በማቀናጀት፣ የእርስ በእርስ የመረጃ ልውውጣቸውን በማቀላጠፍ ለደንበኞች እርካታ ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል። የጎንደር መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ሕንጻ የከተማዋን ቀደምት የኪነ- ሕንጻ ጥበብ በጠበቀ መንገድ በጥራት ተገንብቶ የተጠናቀቀ መሆኑንም አብራርተዋል። በቀጣይም በኮምቦልቻ፣ በደብረ ማርቆስ እና ደብረ ብርሃን ከተሞች የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ እንደሚጀምሩም ነው የተናገሩት። በ2019 በጀት ዓመትም በክልሉ ሁሉም ወረዳዎች እና ከተሞች የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎትን የማስፋፋት ስራ እንደሚሠራም አመላክተዋል።
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎቱን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እያዘመነ ነው - ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ
Sep 4, 2026 239
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 29/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎቱን ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እያዘመነ መሆኑን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ ገለጹ። የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ደንበኞች በዘመናዊ ዲጂታል አማራጭ የሚገለገሉበት የዲጂታል መተግበሪያ ዛሬ አስመረቋል። የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አብዱልበር ሸምሱ (ኢ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያሳልጥ የባሕር ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል። በዚህም የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለሀገሪቱ የሎጂስቲክስ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት አሰራር እየተገበረ መሆኑን ተናግረዋል። ተቋሙ ለአፍሪካ ብቸኛ እና ታሪካዊ የባህር ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ሆኖ መቆየቱን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅትም ዓለም አቀፍ ደረጃን የሚመጥን አዲስ አሰራር ስርዓት እየተገበረ ይገኛል ብለዋል። ዛሬ የተመረቀው ዲጂታል ቴክኖሎጂ ደንበኞች እንግልት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው እንዲሁም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን የሚያፋጥን እንደሆነ አስታውቀዋል። በቀጣዮቹ ዓመታት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ የሚጠናቀቁ ትላልቅ አዳዲስ ሲስተሞች እየተገነቡ መሆኑን ጨምረው አስታውቀዋል። በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተቋሙን ከዓለም አቀፍ አሰራሮች ጋር እኩል የሚያሰልፉ መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የቦርድ አባልና የኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በበኩላቸው ፤ የሎጂስቲክስ ሥርዓቱን የሚያዘምን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። በዚህም መንግሥት የየብስ ትራንስፖርት፣ የባቡርና የደረቅ ወደብ መሠረተ ልማቶችን ከመገንባት ባለፈ፣ የመርከቦች ቁጥር እንዲበራከት እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ አቅም ለማጎልበት ከሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች በተጨማሪም የባሕር በር ባለቤትነት ምላሽ ለማረጋገጥ በዋና አጀንዳነት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ የተመረቀው ዲጂታል ቴክኖሎጂም አገልግሎቱን ይበልጥ ለማሳለጥ ትልቅ ጥቅም እንደሚሰጥ አስታውቀዋል። የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቅልጥፍናን ለማሳለጥ የቴክኖሎጂ አሠራር ወሳኝ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍራሆል ጣፋ ናቸው። የኢትዮጵያ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂንና የሎጂስቲክስ ዘርፍ ስትራቴጂን መሠረት በማድረግ የሎጂስቲክስ ዘርፉን ለማዘመንና አሠራሩን ዲጂታላይዝ የሚያደርጉ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የዲጂታል መተግበሪያውም ግልጽ፣ ፈጣንና ዘመናዊ አሠራር ሥርዓትን ለመገንባት የሚያስችል ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢንስቲትዩቱ የሀገሪቱን የልማት ጉዞ የሚያፋጥን የሰው ሃይል የማፍራት ድርሻውን ያጠናክራል
Sep 4, 2026 204
ሃዋሳ ፤ነሐሴ 29/2018 (ኢዜአ) ፡-የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ገበያ መር አዳዲስ ፕሮግራሞች በመክፈት የሀገሪቱን የልማት ጉዞ የሚያፋጥን የሰው ሃይል የማፍራት ድርሻውን እንደሚያጠናክር አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ በ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና በቀጣይ እቅዶችና አቅጣጫዎች ላይ በሃዋሳ መክሯል።   የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት ኢንስቲትዩቱ ገበያ መር የሆኑ 11 አዳዲስ ፕሮግራሞችን በመክፈትና የተማሪዎች የቅበላ አቅሙን በማሳደግ የሀገሪቱን የልማት ጉዞ የሚያፋጥን የሰው ሃይል በማፍራት የበኩሉን እየተወጣ ነው ። ለዚህም አቅርቦት መር የነበረውን የስልጠና ሂደት ወደ ፍላጎት መር በመቀየር ዘመኑን የዋጁ የስልጠና ፕሮግራሞች ላይ እየተሰራ ነው ብለዋል። በሳይበር ሴኩሪቲ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና በባዮ ሜዲካል ቴክኖሎጂ ጥናትን መሰረት በማድረግ የስልጠና ዘርፎች መከፈታቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። ኢንስቲትዩቱ የጥናትና ምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንተርፕራይዝ ልማት ተግባራቱን ለማሳካት ከ17ዐ በላይ ኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር መፈጠሩንም አመልክተዋል። በበጀት አመቱም ከ40 በላይ የምርምር ስራዎችን በማድረግ ለፖሊሲ ግብአትና ለቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲያግዙ እንዲሁም ተኪ ምርቶችን ለማምረት አቅም የመፍጠር ስራ መሰራቱን ጠቁመዋል። በቀጣይም በኢንስቲትዩቱ የ10 አመት ስትራቴጂክ እቅድ ላይ መሰረት በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ችግር ፈቺ የፈጠራ ማእከላት የማድረጉ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።   በምክትል ከንቲባ ማእረግ የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሃላፊ አቶ ቸርነት ፍላቴ በበኩላቸው በከተማው በተከናወኑ በርካታ የመሰረተ ልማት ስራዎች የቴክኒክና ሙያ ተቋማትና ባለሙያዎች በፈጠራ ስራ ጉልህ ድርሻ አበርክተዋል ብለዋል። የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ያወጧቸው የሰው ሀይልና የምርምር ስራዎች በከተማዋ እድገት የራሳቸውን ድርሻ ማበርከታቸውን ጠቁመዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል በኢንስቲትዩቱ የቴክስታይልና አፓሬል ፋሽን ቴክኖሎጂ ፋካሊቲ ዲን መረርቱ ዋቁማ (ዶ/ር) እንደገለፁት ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን የሰው ሃይል ለማፍራት በመደበኛና በአጫጭር ስልጠናዎች በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። ፋሽን ቴክኖሎጂው የሚፈልገውንና ዘመኑን የዋጁ ፕሮግራሞችን በመክፈት የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር ከዘርፉ የሚገኙ ጥቅሞችን የማሳደጉ ስራ እንደሚጠናከር አመላክተዋል ። በመድረኩ በቀረቡ የውይይት መነሻ ሰነዶችና የተቋሙ የ10 አመት ስትራቴጂክ እቅድ ላይ ውይይት ተደርጓል።          
ስፖርት
አርሰናል ከቼልሲ፡ የሳምንቱ ተጠባቂ የሊግ ጨዋታ
Sep 6, 2026 199
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ):- በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከቼልሲ ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። የለንደን ደርቢ ጨዋታ ምሽት 12፡30 ላይ በኤምሬትስ ስታዲየም ይካሄዳል። አርሰናል እና ቼልሲ በተመሳሳይ በስድስት ነጥብ፣ በግብ ክፍያ ተበላልጠው ሶስተኛና አራተኛ ደረጃን ይዘዋል። ባለሜዳው አርሰናል በሁለቱ የሊግ ጨዋታዎች አራት ግቦችን ሲያስቆጥር ምንም ግብ አላስተናገደም። ይህም የቡድኑን፣ በተለይም የተከላካይ መስመሩን ጥንካሬ የሚያሳይ ነው። ተጋጣሚው ቼልሲ በሁለት ጨዋታዎች ሰባት ግቦችን ከመረብ ሲያሳርፍ አምስት ግቦች ተቆጥረውበታል። ቼልሲ የማጥቃት እንቅስቃሴው ጥሩ የሚባል ቢሆንም በተከላካይ ክፍሉ ላይ ያሉ ድክመቶችን ማረም ይኖርበታል። ሁለቱ የለንደን ተቀናቃኝ ክለቦች በሊጉ ሲገናኙ የአሁኑ ለ69ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 68 ጨዋታዎች አርሰናል በ28ቱ ድል ሲቀናው፣ ቼልሲ 20 ጊዜ አሸንፏል። በቀሪ 18 ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። በነዚህ ጨዋታዎች አርሰናል 97 ግቦችን ከመረብ ሲያሳርፍ፣ ቼልሲ በበኩሉ 85 ጎሎችን አስቆጥሯል። ባለፉት አምስት የሊግ ግንኙነታቸው አርሰናል በሶስቱ ሲያሸንፍ፣ በቀሪዎቹ ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርተዋል። ቼልሲ ለመጨረሻ ጊዜ አርሰናልን በሊጉ ያሸነፈው እ.አ.አ በ2021 ነው። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ አርሰናል በአዲሱ የውድድር ዓመት ያደረጋቸውን ሁለት ጨዋታዎች በማሸነፍ ክብሩን የማስጠበቅ ጉዞውን በጥሩ ሁኔታ ጀምሯል። ተጋጣሚው ቼልሲም ሁለቱን የሊግ ጨዋታዎች በድል በመወጣት መልካም ጅማሮ አድርጓል። በመሆኑም የሁለቱ የለንደን ክለቦች ጨዋታ ጠንካራ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል። የ41 ዓመቱ ክሪስ ካቫናግ ተጠባቂውን ፍልሚያ በዋና ዳኝነት ይመሩታል። በሌላኛው መርሐ ግብር ኤቨርተን ከማንችስተር ዩናይትድ በሂል ዲኪንሰን ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ኤቨርተን ከሁለት ጨዋታዎች ማግኘት የቻለው አንድ ነጥብ ብቻ ሲሆን፣ ተጋጣሚው ማንችስተር ዩናይትድ ሶስት ነጥብ አለው። ባለሜዳው ኤቨርተን በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን ለማስመዝገብ ወደ ሜዳ ይገባል። በሁለተኛው ሳምንት ኤፕስዊች ታውንን 5 ለ 2 የረታው ማንችስተር ዩናይትድ ደግሞ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ይፋለማል። ጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል።
አካባቢ ጥበቃ
አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ በመቀየስ ረገድ መሪ ሚና መጫወት ይገባታል-ክላቨር ጋቴቴ
Sep 7, 2026 127
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 2/2018 (ኢዜአ)፦ አፍሪካ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ድርድሮችና መፍትሔዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የጎላ ሚና መጫወት እንዳለባት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ፡፡ 14ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። ጉባኤው "ከተስፋ ቃል ወደ ተግባር፤ የቤሌም-አንታልያ-አዲስ አበባ ፍኖተ ካርታ" በሚል መሪ ሐሳብ ነው እየተካሄደ ያለው። የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክላቨር ጋቴቴ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፣ አፍሪካ ለዓለም አቀፍ የካርቦን ልቀት የምታበረክተው አስተዋጽኦ አራት በመቶ ቢሆንም የችግሩን ከባድ መዘዝ እየተሸከመች ትገኛለች። ሆኖም ይህ እውነታ ለአፍሪካ የተጎጂነት ታሪክ ብቻ ሆኖ ሊቀጥል እንደማይገባ ተናግረው አፍሪካ ያላትን ከፍተኛ የታዳሽ ኃይል አቅም፣ የማዕድን ሀብቶች፣ ወጣት የሰው ኃይል እና እያደገ ያለውን ገበያ በመጠቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ መፍትሔዎችን በመቀየስ ረገድ መሪ ሚና መጫወት እንዳለባት ገልጸዋል። አፍሪካ እስከ እ.ኤ.አ 2030 ድረስ የተቀመጡ የአየር ንብረት ግቦችን ለመተግበር በየዓመቱ 277 ቢሊዮን ዶላር የሚያስፈልጋት ቢሆንም እያገኘች ያለችው ከፍላጎቷ 11 በመቶ ያህሉን ብቻ ነው ብለዋል። የአየር ንብረት እርምጃዎች ከኃይል ተደራሽነት፣ከኢንዱስትሪ ልማት እና ከሥራ እድል ፈጠራ ጋር ተያይዘው መከናወን እንዳለባቸው አሳስበዋል። ከ600 ሚሊዮን በላይ አፍሪካውያን አሁንም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ያላገኙ በመሆናቸው የታዳሽ ኃይልን ማስፋፋት የኢኮኖሚው መሠረት ሊሆን ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣናን በመጠቀም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ሀብቶች ላይ እሴት በመጨመር አህጉራዊ የእሴት ሰንሰለት መገንባት ይቻላል ሲሉም ገልጸዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ስኬቶችን በማላቅ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቷል- ከንቲባ ከድር ጁሃር
Sep 6, 2026 148
ድሬዳዋ፣ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡- የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ስኬቶችን በማላቅ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የአየር ንብረት ለውጥ ሚዛንን ለመጠበቅ ትኩረት መሰጠቱን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። የእምርታ ቀን በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ በመትከልና እና በሌሎች ዝግጅቶች በድሬዳዋ እየተከበረ ነው። "እምርታ ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሃሳብ በክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ ፓርክ የችግኝ ተከላ መርሀግብር ተካሂዷል።   ከንቲባ ከድር ጁሃር በወቅቱ እንደተናገሩት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችን በማላቅ ለምግብ ዋስትና መረጋገጥና የአየር ሚዛን ለመጠበቅ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። የመደመር መንግስት ባለፉት ዓመታት ተግባራዊ ካደረጋቸው እና የአገር የከፍታ ጉዞ ዕውን ከሆኑባቸው ተግባራት መካከል አንዱ የአረንጓዴ አሻራ መሆኑን አንስተዋል። በድሬዳዋ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሮች ችግኞች የአካባቢውን ስነምህዳር በመለወጥ፣ የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጨምር በማገዝና የተመናመነውን ደን በመመለስ ወሳኝ ሚና ማበርከታቸውን አስታውቀዋል። በተለይ በድሬዳዋ ሲከሰት የነበረን የጎርፍ አደጋን በላቀ ደረጃ በመቀነስና ውሃን ወደ ጥቅም ለመለወጥ እያበረከተ ያለው አስተዋፅኦ ለማስቀጠል ችግኞች በላቀ ህዝባዊ ተሳትፎ እየተተከሉ ይገኛሉ ብለዋል።   ዛሬም በእምርታ ቀን በህዝብ እና በአመራሩ ተሳትፎ የተተከሉት ችግኞች የተገኘውን እመርታ ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸው አንስተዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በበኩላቸው እንዳሉት፣ የእምርታ ቀን በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የተገኙ ውጤቶችን በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል መደላድል የተፈጠረበት ነው። በተለይ መርሀግብሩ የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውሀ ሀብት እንዲያድግ መሰረት በመጣሉ የገጠሩ ህብረተሰብ አነስተኛ መስኖ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን በመጨመር ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር እያገዘ ይገኛል ብለዋል። የእምርታ ቀንን ምክንያት በማድረግ ዛሬ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ላይ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ ሆነዋል።  
አረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን በመከላከል ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ነው - የአፍሪካ ህብረት
Sep 5, 2026 235
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖዎችን ለመመከትና ለብዝሃ ህይወት ጥበቃ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ ከባቢና ብሉ ኢኮኖሚ ዳይሬክተር ሃርሰን ንያምቤ ገለጹ። ዳይሬክተሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አረንጓዴ አሻራ ንጹህ አየርን ጨምሮ ሌሎች ስነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን ከማስገኘቱም በላይ፣ የካርበን ልቀትን በመቀነስ የአየር ሙቀት መጨመርን ለመከላከል እንደሚያስችል ተናግረዋል። የተራቆተ መሬትንና የአካባቢ ስነ ምህዳር እንዲያገግም በማድረግ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳትን ለመከላከል እየተደረገ ባለው ጥረት ውስጥ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በጥቅሉ ሲታይ የአረንጓዴ አሻራ በርካታ ሁለገብ ጥቅሞች ያሉት ሀገራዊ ኢኒሼቲቭ መሆኑንም አንስተዋል። የአፍሪካ ሀገራት በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ተግባራት ላይ የልምድ ልውውጥ ማድረግ እንደሚገባቸው የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ በዚህ ረገድም በአካባቢ ጥበቃ ላሉባቸው ተግዳሮቶች መፍትሄ ለማበጀት ከኢትዮጵያ ተሞክሮ መውሰድ እንደሚችሉ ነው የገለጹት። ኢትዮጵያም ስኬታማ ተሞክሮዎቿን ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በማካፈል ግንባር ቀደም ሚና መጫወት እንዳለባት ዳይሬክተሩ አንስተዋል።
‎የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ልምድ ለማካፈል ወጣቶች ወደተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሊያቀኑ ነው
Sep 2, 2026 462
‎አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ልምድ ለማካፈል ወጣቶች ወደተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሊያቀኑ መሆኑ ‎የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አባንግ ኩመዳን ገለጹ። ከመላው የሀገሪቱ የተውጣጣ የወጣቶች ቡድን በሦስት የአፍሪካ ሀገራት ነገ የሚጓዝ ይሆናል። ‎የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አባንግ ኩመዳን እንደገለጹት፤ ወጣቶቹ የሚጓዙት ጋና፣ ዚምባብዌና ናይጄሪያ ነው። በዚህ የጉዞ መረሃ ግብር ሀያ አራት ወጣቶች የሚሳተፉ ሲሆን፤ የተለያዩ ዝርያ ያላቸው ችግኞችን በመትከል ልምድ እንደሚያካፍሉም አስታውቀዋል። ‎መርሃ ግብሩ ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄድ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ ቀደም የብልጽግና ወጣት ክንፍ በፓኪስታን የችግኝ ተከላ ማካሔዳቸውን ገልጸዋል። ‎የልዑካኑ ጉዞ የልምድ ልውውጥ ከማድረግ በተጨማሪ ወንድማማችነትን ለማጠናከር የሚያግዙ ተግባራትን እንደሚያከናውን አስታውቀዋል። ‎በቀጣይም ወጣቶች ወደ ተለያዩ ሀገራት በመሄድ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በማከናወን የኢትዮጵያን ልምድ የማካፈል ተግባርን ያጠናክራል ብለዋል። ‎በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በስኬታማነት እየተከናወነ ይገኛል። ‎በዚህ ዓመት ብቻ ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞች በአንድ ጀምበር መተከላቸው ይታወሳል። ‎ይህ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ዓለም አቀፍ እውቅና እያገኘ ሲሆን የተለያዩ ሀገራትም ተሞክሮውን እየወሰዱት ይገኛሉ።  
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ አጋርነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Sep 4, 2026 327
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 29/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን እና ሁሉን አቀፍ ትብብራቸውን የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ውይይቱ በአፍሪካ ህብረትና አሜሪካ መካከል ያለውን ለረጅም ጊዜ የቆየ አጋርነት ማጠናከር እና በአህጉሪቱ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። የኮሚሽኑ ሊቀመንበር የአፍሪካና አሜሪካን ትብብር ታሪካዊ መሆኑን አውስተው በህብረቱ፣ በአባል ሀገራት እና በአሜሪካ መካከል የሁለቱንም ወገኖች ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ ጠንካራ አጋርነት መገንባት እንደሚገባ አሳስበዋል። በምስራቅ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሱዳን እየተደረጉ ላሉ አፍሪካ መር የሰላም ጥረቶች አሜሪካ እያደረገች ላለው ገንቢ አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያ በበኩላቸው አፍሪካ አሜሪካ ቀዳሚ ትኩረት የምትሰጣት አህጉር እንደሆነች ገልጸዋል። የጋራ ፍላጎቶችንና ግቦችን ከህብረቱ ኮሚሽንና ከአባል ሀገራት ጋር በመሆን ለማሳካት ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ በዲፕሎማሲ፣ እንዲሁም በሰላምና ጸጥታ ያለውን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባም አመልክተዋል። በውይይቱ ላይ በሱዳን ጉዳይ አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ የሰብአዊ እርዳታ ያለ ገደብ እንዲገባ እና በሲቪሎች የሚመራ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመር አጽንዖት ተሰጥቷል። በአፍሪካ ባለቤትነት የሚመሩ የሰላም ጥረቶች እና አሜሪካ የምትደግፋቸው የሰላም ሂደቶች በተቀናጀ መልኩ ለመተግበር ከስምምነት ላይ ተደርሷል። በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመሰረተ ልማት እና በሰላም መስኮች የሁለቱን ወገኖች ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ የትብብር መስኮች ተገምግመዋል። ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ህብረትና በአሜሪካ ስትራቴጂክ ኢንቨስትመንት ማዕቀፍ ውስጥ የተደረጉ ስምምነቶችን ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። በሊቢያ ጉዳይ ዘላቂ የፖለቲካ መፍትሄ ማግኘት እንደሚያስፈልግም ተነስቷል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር እና ረዳት ሚኒስትሩ የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከርና የትብብር አድማሱን ለማስፋት የጋራ ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 1673
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 1328
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች።   ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 1603
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሐተታዎች
የስኬት መገለጫና የውጤት ማሳያዎች
Aug 28, 2026 507
አዲስ አበባ ነሀሴ 22/2018 (ኢዜአ) የስኬት መገለጫና የውጤት ማሳያዎች በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብና የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (Homegrown Economic Reform) እቅዶችን በመተግበር በበርካታ ዘርፎች መሠረታዊ ለውጦችን እና ስኬቶችን ማስመዝገብ ተችሏል። በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጂታል (አይሲቲ)፣ በማዕድን እና በቱሪዝም ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብታዊ አቅም ከማሳደግ ባሻገር የወደፊት ዘላቂ እድገት መሠረት ያኖሩ መሆኑን መናገር ይቻላል። በመሆኑም በአምስቱ ዋና ዋና ሴክተሮች የመጡ ውጤቶችና የተመዘገቡ ስኬቶችን በወፍ በረር እንቃኛለን። 1. በግብርና ዘርፍ የስንዴ ምርትና የውጭ ኤክስፖርት: የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት መስፋፋት ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሰረት አስቀምጧል። ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የስንዴ ምርትን ወደ ውጭ ሀገር መላክ የቻለችበትን እመርታዊ ስኬትም አሳይቶናል። የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭን በመተግበር በወተት፣ በእንቁላል፣ በዶሮና የማር ምርት እንዲሁም በአትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ሩዝና ሻይ ልማትም ባለፉት አምስት አመታት እመርታዊ ለውጥ ተመዝግቧል። አርሶ አደሩ የመሬትና የውሃ ሀብቶችን አቃፊ በሆነ መንገድ በመጠቀም በዓመት ሁለትና ሶስት ጊዜ ማምረት የሚችልበት አሰራር ተዘርግቷል። በዚህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ሁነኛ የገቢ ምንጭ የሆነበትን እድል ፈጥሯል። ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን የመቻል አቅም በመገንባት ላይ ይገኛል። በተለይም ደግሞ የቡና ምርታማነትና ጥራት በማደጉ ምክንያት በኤክስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማገኘት ተችሏል።   በዘርፉ በቀጣይም የግብርናውን ዘርፍ ይበልጥ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በሜካናይዜሽን በማስደገፍ ምርታማነትን የማሳደግ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። የመስኖ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት የዝናብ ጥገኝነትን ለመቀነስ መጣር እንዲሁም የግብርና ምርቶችን ጥራት በማሻሻልና በማቀነባበር ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ዋጋ ማሳደግ ተገቢ ይሆናል። 2. የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሀገራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ንቅናቄ በመፍጠር ቀደም ሲል ተቆልፈው የነበሩና በዝቅተኛ አቅምያመርቱ የነበሩ ፋብሪካዎች ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲመለሱ ተደርጓል። የሀገር ውስጥ የምርት ፍላጎትን በመሸፈን ለውጭ ሀገር ምርቶች ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪም መቀነስ አስችሏል። ለሀገር ውስጥና ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ የህግና የአሰራር ሁኔታዎችን በመፍጠር በርካታ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ ተችሏል። ከተገነቡት የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያ ፓርኮች (IAIPs) ጋር አርሶ አደሩን በማስሳሰር የግብአትና የምርት ትስስር እንዲጠናከር ተደርጓል። የአምራች ዘርፉ መስፋፋት ለብዙ ሺህ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች የሥራ እድል መፍጠር የታቸለበት ሆኗል። በቀጣይም የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በኃይል፣ በሎጂስቲክስና በግብአት አቅርቦት ሙሉ በሙሉ በመደገፍ ኤክስፖርትን ማሳደግ። የአምራች ኢንዱስትሪዎች 80% እና ከዚያ በላይ የሀገር ውስጥ ጥሬ ዕቃዎችን እንዲጠቀሙ ማበረታታት፣ በህዝብና በግል አጋርነት (PPP) አማካኝነት በትልልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ላይ የግሉን ዘርፍ አሳትፎ ማስፋፋት ትኩረት የሚደረግበት ይሆናል።   3. የዲጂታል (አይሲቲ) ዘርፍ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" ስልት ስኬቶችን በማስቀጠል ወደ "ዲጂታል 2030" እቅድ መሸጋገር ተችሏል። በ"መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በሌሎች ፖርታሎች አማካኝነት ህዝባዊ አገልግሎቶችን በበይነ-መረብ (Online) የመስጠት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የዜጎችን መረጃ ማዕከላዊ የሚያደርግና ለፋይናንስ እንዲሁም ለሌሎች አገልግሎቶች መሠረት የሆነውን የፋይዳ መታወቂያ ፕሮጀክት በላቀ መልኩ ማሳካት ተችሏል። የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን የኮደር ስልጠናም የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ ታላቅ ሀገራዊ የስልጠና መርሃ ግብር ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።የዲጂታል አገልግሎቶች መዘርጋታቸው የፊት ለፊት ግንኙነትን በመቀነስ ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን በመከላከል የኢንቨስትመንት ምህዳሩን አሳልጧል። የቴሌኮም ዘርፍ ውድድር: የቴሌኮም ዘርፉን ክፍት ማድረግን ተከትሎ የኢንተርኔትና የኔትወርክ ተዳራሽነትንና ጥራትን በየገጠሩ የማስፋት ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቶችን እና የባንክ አገልግሎቶችን ይበልጥ ዘመናዊና የተቀናጁ ማድረግም አስፈላጊ ይሆናል። የሀገሪቱን የዲጂታል መሠረተ ልማት ከሳይበር ጥቃቶች የመጠበቅ አቅምን ማጠናከር። 4. የማዕድን ዘርፍ በዘርፉ ይስተዋል የነበረውን ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ በመግታት ህጋዊ አሰራርና ቁጥጥር እንዲሰፍን ተደርጓል። የህግና መመሪያዎች ማሻሻያ በማድረግ የማዕድን ዘርፉን ለውጭና ሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ማራኪ የሚያደርጉ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ተደርገዋል። የወርቅ፣ የከሰል ድንጋይ፣ የሲሚንቶ ግብአቶችና የከበሩ ድንጋዮች ምርትን በማሳደግ ዘርፉ የሀገሪቱ ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ እንዲሆን ተሰርቷል። በተለይም የከሰል ድንጋይ ምርትን በሀገር ውስጥ አምርቶ በመተካት ለፋብሪካዎች ግብአት ማቅረብ ተችሏል። 5. የቱሪዝም ዘርፍ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ( ዶ/ር)አነሳሽነት የተጀመሩት "ገበታ ለሸገር"፣ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች በመላ ሀገሪቱ በርካታ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን መገንባት ተችሏል። በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች የተከናወኑ የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበትና ለኑሮ ምቹነት ከመጨመራቸው ባሻገር ለከተማ ቱሪዝም ትልቅ እድል ፈጥረዋል። አዲስ አበባ በርካታ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችንና ኮንፈረንሶችን ባካሄደችበት የዲፕሎማሲና የኮንፈረንስ ማዕከልነቷን አጠናክራለች።   የሀገሪቱን ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች የመጠበቅ፣ የማደስና ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራዎች በስፋት ተከናውነዋል። በድምሩ ባለፉት አምስት ዓመታት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጂታል፣ በማዕድን እና በቱሪዝም ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች ሀገሪቷን ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ምዕራፍ ማሸጋገር አስችለዋል። በመሆኑም እነዚህን ስኬቶች አጠናክሮ ለማስቀጠል የታቀዱትን የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች በተቀናጀ መልኩ መተግበር፣ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ እና የግሉን ዘርፍ አሳታፊነት ማሳደግ በቀጣይ አዲስ የሚመሰረተው መንግስት ዋነኛ የቤት ስራ ይሆናል።  
የአረንጓዴ አሻራ ስኬት፦ኢትዮጵያን የአየር ንብረት ጥበቃ ሞዴል ያደረገ ኢኒሼቲቭ
Aug 23, 2026 618
የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ የተጀመረው በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ነው። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እስከ አሁን ከ54 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እ.አ.አ በ2027 በኢትዮጵያ በሚካሄድበት ወቅት የተተከሉ ችግኞችን ብዛት 65 ቢሊዮን የማድረስ እቅድ ተይዞ እየተሠራ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች ያሉት ነው።ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የምግብ ምርታማነትን በማሳደግ፣ የደን ሽፋንን በመጨመር፣ የተራቆተ መሬትን ወደ ነባር ይዞታው እንዲመለስ በማድረግ እና አይበገሬ የአረንጓዴ ኢኮኖሚን በመገንባት ረገድ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። በዚህም በ2011 ዓ.ም 17.2 በመቶ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን፣ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በተከናወነው ሥራ ወደ 23.6 በመቶ ማደግ ችሏል።   ይህ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እውቅና አግኝቷል።በሁለተኛው የዓለም የምግብ ሥርዓት ጉባኤ እንዲሁም በአዲስ አበባ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ ሥራዋን ያስተዋወቀች ሲሆን፣ የአፍሪካ ሀገራትም ለአህጉሪቱ ትልቅ ተምሳሌት የሚሆን ኢኒሼቲቭ ሲሉ አድንቀውታል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታዘጋጅ መመረጧ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል እያከናወነች ላለው ጥረት ዓለም አቀፍ እውቅና የተሰጠበት እና የሀገሪቱን የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ውጤት የሚያሳይ ነው። ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ችግኞችን በመለገስ የአካባቢ ጥበቃ የጋራ አጀንዳ መሆኑን በተግባር አሳይታለች።ይህም አረንጓዴ ዲፕሎማሲ በሀገራት መካከል በጎ ግንኙነትንና አዎንታዊ የቀጣናዊ ትስስር ድልድይን እየገነባ ይገኛል። የድንበር ተሻጋሪ የወንዝ ተፋሰሶችን በመንከባከብ፣ የታዳሽ ኃይል አቅርቦትን ለጎረቤት ሀገራት በማዳረስ እና በጋራ ድንበሮች አካባቢ የደን ሽፋንን በማሳደግ ረገድ እያከናወነችው ያለው ሥራ አህጉራዊ ሰላምና ትብብርን የሚያጎለብት አዲስ የዲፕሎማሲ መንገድ ከፍቷል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች የአህጉሪቱን ፍላጎትና ጥቅም ለማስከበር ግንባር ቀደም ተሟጋች ሆናለች።   ለአየር ንብረት ለውጥ አነስተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ነገር ግን ለጉዳቱ በከፍተኛ ሁኔታ የተጋለጡ የአፍሪካ ሀገራት ፍትሃዊ የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ እንዲያገኙ ድምፅ በመሆን አህጉራዊ መሪነቷን አስመስክራለች። ይህም አፍሪካውያን በራሳቸው ሀገር በቀል መፍትሔዎች የአየር ንብረት ጥበቃን ማረጋገጥ እንደሚችሉ ማረጋገጫ ሆኗል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና አምባሳደሮች የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ልማት እንቅስቃሴ ለአካባቢ ጥበቃ አርአያ የሚሆን ዓለም አቀፍ ሞዴል ሲሉ አድንቀውታል።   ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን ከመጠቀም፣የካርቦን ልቀትን ከመቀነስ እና ከኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መስፋፋት ጋር አጣጥማ የምታካሂደው እንቅስቃሴ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች ላይ እውቅና እንድታገኝ አስችሏታል።
ረብጣ ገንዘብ ከወጣባቸው ዝውውሮች እስከ አነጋጋሪ የህግ ለውጦች ፡ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲሱ የውድድር ዓመት ምን ይዞ መጣ?
Aug 21, 2026 617
በሙሴ መለሰ የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪያን በጉጉት የሚጠብቀው የ2026/27 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ዛሬ በይፋ ይጀምራል። የዘንድሮው የውድድር ዘመን በሰኔ እና ሐምሌ ወራት የተካሄደውን የ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ተከትሎ፣ ለተጫዋቾች በቂ የእረፍት ጊዜ ለመስጠት ሲባል ከተለመደው አንድ ሳምንት ዘግይቶ እንዲጀምር ተደርጓል። የመክፈቻው ጨዋታ በኢምሬትስ ስታዲየም የባለፈው የውድድር ዘመን ሻምፒዮን አርሰናል እና ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ሊጉ በተመለሰው ኮቨንትሪ ሲቲ መካከል ምሽት አራት ሰዓት ላይ በኤምሬትስ ስታዲየም ይካሄዳል። ይህ አዲስ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት በክረምቱ የተጫዋቾች ዝውውር መስኮት ላይ የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች ከፍተኛ ተሳትፎ አድርገዋል። እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት፣ የሊጉ ክለቦች ለተጫዋቾች ዝውውር ብቻ ከ2.14 ቢሊዮን ፓውንድ በላይ ወጪ አድርገዋል። ይህ የወጪ መጠን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከሌሎች የአውሮፓ አራት ታላላቅ ሊጎች (ስፔን፣ ጣልያን ጀርመንና ፈረንሳይ) በጥምረት ካወጡት የገንዘብ መጠን በላይ ሆኗል። ሞርጋን ሮጀርስ ከአስቶን ቪላ ወደ ቼልሲ በ117 ሚሊዮን ፓውንድ በመዘዋወር የክረምቱ ውዱ ተጫዋች መሆን ችሏል። ኤሊዮት አንደርሰን ከኖቲንግሃም ፎረስት ወደ ማንቸስተር ሲቲ በ116 ሚሊዮን ፓውንድ አምርቷል። በተጨማሪም ሳንድሮ ቶናሊ ከኒውካስል ወደ ቶተንሃም በ100 ሚሊዮን ፓውንድ፣ እንዲሁም ብሩኖ ጉማሬሽ ከኒውካስል ዩናይትድ ወደ አርሰናል በ75 ሚሊዮን ፓውንድ መዘዋወራቸው የክረምቱን የዝውውር ገበያ ከሚጠቀሱ ዝውውሮች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ከዝውውር ወጪው ባሻገር፣ የዘንድሮው የውድድር ዘመን በአዳዲስ አሰልጣኞች የታጀበ ሆኗል። በሊጉ ታሪክ ከፍተኛው በተባለ ደረጃ ዘጠኝ ክለቦች ውድድሩን በአዲስ አሰልጣኞች ይጀምራሉ። ፔፕ ጋርዲዮላ ማንቸስተር ሲቲን በገዛ ፈቃዱ መልቀቁን ተከትሎ የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አሁን ላይ በሊጉ ረጅም ጊዜ (ሰባት ዓመታት) የቆየው አሰልጣኝ ሆኗል። የቼልሲው ዣቢ አሎንሶ፣ የማንቸስተር ሲቲው ኤንዞ ማሬስካ እና የሊቨርፑሉ አንዶኒ ኢራኦላ ከአዳዲሶቹ አሰልጣኞች መካከል ይጠቀሳሉ። ማይክል ካሪክ በማንቸስተር ዩናይትድ እንዲሁም ሮቤርቶ ዴ ዜርቢ በቶተንሃም ሆትስፐርስ የመጀመሪያ ሙሉ የውድድር ዓመታቸውን ይጀምራሉ። የሊጉ የተሳታፊዎች ስብጥርን በተመለከተ፣ ኮቨንትሪ ሲቲ ከ25 ዓመታት በኋላ ከሃል ሲቲ እና ኢፕስዊች ታውን ጋር በመሆን ከታችኛው ሊግ አድገው ሊጉን ተቀላቅለዋል። በተቃራኒው ዌስትሃም ዩናይትድ፣ በርንሌይ እና ዎልቨርሃምፕተን ዋንደረርስ ባለፈው የውድድር ዘመን መውረዳቸው የሚታወስ ነው። በተጨማሪም የእንግሊዝ ክለቦች ባለፈው ዓመት በአውሮፓ ባሳዩት አስደናቂ ብቃት ምክንያት፣ በዚህ የውድድር ዘመን ክብረ ወሰን የሆነ ዘጠኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በአውሮፓ ውድድሮች ላይ ይሳተፋሉ። አርሰናል፣ አስቶንቪላ፣ ሊቨርፑል፣ ማንቸስተር ሲቲ እና ማንቸስተር ዩናይትድ በሻምፒዮንስ ሊግ የሚወዳደሩ ሲሆን፣ በርንማውዝ፣ ሰንደርላንድ እና ክሪስታል ፓላስ በዩሮፓ ሊግ እንዲሁም ብራይተን በኮንፈረንስ ሊግ አገራቸውን ይወክላሉ። የሊጉ አስተዳደር የክለቦችን የፋይናንስ ወጪ የሚቆጣጠር አዲስ የወጪ ገደብ (Squad Cost Ratio) መመሪያን ተግባራዊ አድርጓል። በዚህም መሠረት ክለቦች ለተጫዋቾች ደሞዝ እና ለዝውውር የሚያወጡት ጠቅላላ ወጪ ከገቢያቸው 85 በመቶ እንዳይበልጥ ተወስኗል። ህጉን የሚጥሱ ክለቦችም የነጥብ ቅነሳ ቅጣት ይገጥማቸዋል። የጨዋታ ፍጥነትን ለመጨመርና ሰዓት ማባከንን ለመግታት በርካታ አዳዲስ የዳኝነት ህጎች በይፋ ስራ ላይ ይውላሉ። በእጅ ውርወራ (Throw-in) እና በመልስ ምት (Goal-kick) ላይ ሰዓት ለሚያባክኑ ተጫዋቾች ዳኛው አምስት ሴኮንድ የሚቆጥር ሲሆን፣ ጊዜ ካለፈ እጅ ውርወራው ለተቃራኒ ቡድን ይሰጣል፤ የመልስ ምት ላይ ከሆነ ደግሞ የተቃራኒ ቡድን የማዕዘን ምት ያገኛል። ሌላው ሰዓት ማባከንን ለመቆጣጠር የወጣው ህግ ተጫዋቾች ታክመው ከወጡ በኋላ ወደ ሜዳ ለመመለስ ቢያንስ አንድ ደቂቃ ውጭ እንዲጠብቁ የሚያስገድደው ደንብ ነው። በተጨማሪም ተጫዋቾች በሚቀየሩበት ወቅት ከሜዳ ለመውጣት የ10 ሴከንድ ገደብ የተጣለባቸው ሲሆን፣ ይሁንና ጊዜው ካለፈ ተቀያሪው መግባት የሚችለው ጨዋታው በሚቀጥለው ጊዜ ሲቆም ብቻ ይሆናል። በዚህ የውድድር ዘመን የቪዲዮ ረዳት ዳኛ (VAR) ውሳኔዎችን ይበልጥ ግልፅ ለማድረግ ትልቅ ማሻሻያ ተደርጓል። አንድ ተጫዋች በሁለተኛ ቢጫ ካርድ ከሜዳ ሲሰናበት አጠራጣሪ ከሆነ ቫር ጣልቃ የመግባት ስልጣን ተሰጥቶታል፤ እንዲሁም በጨዋታ ወቅት በቫር እና በሜዳ ላይ ዳኛው መካከል የሚደረጉ የድምፅ ውይይቶች በሊጉ የጨዋታ ማዕከል በኩል ለደጋፊዎች በቀጥታ ይፋ ይደረጋሉ። በአጠቃላይ፣ የዘንድሮው የ2026/27 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ከአዳዲስ የህግ ለውጦች፣ ከከፍተኛ የዝውውር ወጪዎች እና አዳዲስ የአሰልጣኞች ሹመት ጋር ተያይዞ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረትን ስቧል። አርሰናል የዋንጫ ክብሩን ለማስጠበቅ፣ ማንቸስተር ሲቲ ያለ ፔፕ ጋርዲዮላ አዲስ ምዕራፍ ለመጀመር፣ እንዲሁም አዳዲስ አሰልጣኞችና ክለቦች ህልማቸውን ለማሳካት የሚያደርጉት ፍልሚያ የእግር ኳስ አፍቃሪያን እስከ ግንቦት ወር መጨረሻ ድረስ የሚዘልቅ አስደሳች እና አጓጊ የእግር ኳስ ጊዜን እንደሚያሳልፉ አያጠራጥርም።
ቡሄ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ምስረታ ታሪካዊ ቁርኝት
Aug 19, 2026 813
በሙሴ መለሰ ዛሬ ነሐሴ 13 ቀን የቡሄ በዓል በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ባለበት በዚህ ዕለት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አጀማመሩንና ምስረታውን ከዚህ በዓል ጋር ያለውን የጠበቀ ትስስር ወደ ኋላ መለስ ብሎ የሚታወስበት ነው። የክለቡ ምስረታና የቡሄ በዓል (የሆያ ሆዬ ጨዋታ) ቀጥተኛና የማይነጠል ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፣ ክለቡ በመስረታው ወቅት የነበረበትን የፋይናንስ እጥረት ቀርፎ የመጀመሪያውን ማሊያ ለመግዛት የበቃው በዚህ ዕለት በተሰበሰበ የሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ነበር። የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ቡድን መጀመሪያ ሲጠነሰስ በጆርጅ ዱካስና በአየለ አትናሽ አማካኝነት የነበረ ቢሆንም፣ ክለቡን በይፋ አደራጅቶ ለማቋቋም ግን የግድ የፋይናንስ አቅም ወይም ገንዘብ ያስፈልግ ነበር። ሆኖም ግን በሃገር ፍቅር ስሜት የተነሱት ዘጠኙ ወጣቶች ማለትም አየለ አትናሽ፣ ጆርጅ ዱካስ፣ ዮሐንስ ጥላሁን፣ ገብረመድህን ተፈሪ፣ ተፈራ ገብረእግዚአብሔር፣ ዓለማየሁ እጅጉ፣ መኮንን ደምሴ፣ አስፋው ያዕቆብ እና ክልቱ አያኖ ክለቡን በሚመሰርቱበት ወቅት ቤሳ ቤስቲን እንኳ ኪሳቸው ውስጥ ስላልነበራቸው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ተሰብስበው በሰፊው ተወያዩ። በዚህ የውይይት ወቅት ነው ገንዘብ ለማግኘትና የክለቡን መመስረት እውን ለማድረግ የቡሄ ቀን እጅግ መልካምና ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን የተረዱት። ዘጠኙ ወጣቶች በአንድ ድምፅ ተስማምተው በታሪካዊው የቡሄ ዕለት ማለትም ነሐሴ 13 ቀን 1927 ዓ.ም. በጋራ በመሆን ቡሄ ጨፍረው (ሆያ ሆዬ ብለው) በሚያገኙት ማናቸውም ነገር የክለቡን የመጀመሪያ ማሊያ ለመግዛት ቁርጥ የሆነ ውሳኔ ላይ ደረሱ። በዚያን ጊዜ የነበረው የባህል ልማድ አሁን ካለው የተለየ በመሆኑ፣ ቡሄ ሲጨፈር የሚሰጠው ጥሬ ገንዘብ ሳይሆን ሙልሙል ዳቦ ነበር። በመሆኑም ዘጠኙ ተጫዋቾችና መስራቾች ቀደም ሲል ከሚጨፍሩበትና ለምደውት ከነበረው አካባቢ ራቅ ብለው በመንቀሳቀስ በየቤቱ በር እያንኳኩ በደመቀ ሁኔታ ጨፈሩ፤ በዚህም ጥረታቸው በርካታ ቁጥር ያለው የሙልሙል ዳቦ በአንድነት ማሰባሰብ ቻሉ ታሪካዊውን ስራ ሰሩ። ይሁን እንጂ የተሰበሰበውን ይህንን በርካታ ዳቦ ወደ ጥሬ ገንዘብ ለመቀየር አዲስ አበባ ውስጥ ወደሚገኘው ሰራተኛ ሰፈር ለሚገኙ ወዛደሮች ለመሸጥ ዳቦውን በከረጢት ይዘው ጉዟቸውን ጀመሩ። በዚህ የጉዞ መስመር ላይ ሳሉ ግን ያልተጠበቀ ፈተና ገጠማቸው፤ በመንገድ ላይ ያገኟቸው “ዱርዬዎች” ከተሰበሰበው ዳቦ ላይ የተወሰነውን ነጠቋቸው። ወጣቶቹ ተስፋ ሳይቆርጡ ጉዟቸውን በመቀጠል የተረፈውን ዳቦ ለሰራተኛ ሰፈሩ ወዛደሮች በመሸጥ ማሊያ መግዣ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ በእጃቸው አስገቡ። ከዳቦው ሽያጭ የተገኘችው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን በወቅቱ መገበያያ በትክክል ሁለት ጠገራ ብር ነበረች። የክለባችው የመጀመሪያ መለያ ቡናና ነጭ ነበር። ቡናና ነጭ መሊያን የገዙት ግን ፈልገው አልነበረም በቂ ገንዘብ ስላልነበራቸው በሁለት ጠገራ ብር ከፒያሳ «ግሪካዊ አውግስታስ ዱስ» ከተባለ ሱቅ በርካሽ ስላገኙት ነበር። ይህ በቡሄ ዕለት የተጀመረው ታሪካዊ የማሊያ ግዢ በኋላ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በታህሣሥ ወር 1928 ዓ.ም. በይፋ ተመሠረተ። ክለቡ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለብ በመሆን ታሪካዊ ማዕረግንና ቀዳሚነትን ተቀዳጀ። በ1928 ዓ.ም. በይፋ የተመሰረተው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በታሪኩ የመጀመሪያውን የሜዳ ጨዋታ ያደረገው ከ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ነበር። በዚሁ ታሪካዊ የመጀመሪያ ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚውን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። በዕለቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠንካራ ተፎካካሪ ከነበረው የ"አራራት አርመን" ቡድን ጋር ለመጫወት ወደ ሜዳ ሲያመራ፣ አስቀድመው ከተመረጡትና ቡድኑን ካደራጁት ተጫዋቾች መካከል አንዱ ባልታወቀ ምክንያት ሳይመጣ ቀረ። በዚህ ድንገተኛ መቅረት ምክንያት ቡድኑ በሰው ጎደሎ ለመጫወት በተገደደበት ወሳኝ ሰዓት፣ መስራቾቹ በሜዳው አቅራቢያ መንገድ ላይ ሲጫወት ያገኙትን አንድ ታዳጊ ወጣት ተመለከቱ። ይህ ታዳጊ በወቅቱ ገና የ14 ዓመት ዕድሜ የነበረውና በኋላ ላይ የኢትዮጵያ ስፖርት ባልደረባ የሆነው ይድነቃቸው ተሰማ ነበር። ወጣቶቹም ያለ ምንም ቅድመ ዝግጅት ቡድኑን እንዲሞላ ድንገት ጋበዙት፤ እርሱም የቀረበለትን ጥሪ በደስታ ተቀብሎ በአጋጣሚ ወደ ሜዳ ገባ። ያለ ምንም ልምምድና ዝግጅት በድንገት የተሰለፈው ይድነቃቸው ተሰማ፣ በሜዳ ላይ ያሳየው አስደናቂ ችሎታና ቅልጥፍና ሁሉንም ያስገረመ ነበር። ቅዱስ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ታሪካዊ ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ፣ ለክለቡ የመጀመሪያውን ድል ያስገኙትን ሁለቱንም ታሪካዊ የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ይኸው መንገድ ላይ ተገኝቶ በድንገት የተሰለፈው ታዳጊ ይድነቃቸው ነበር። ይህ ብቃት ገና በታዳጊነቱ በክለቡ ውስጥ ያለውን የማይተካ ቦታ ከማረጋገጡም በላይ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን የድል ጉዞ በደመቀ ሁኔታ እንዲጀመር አድርጓል። ቡሄ በዓል እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ያላቸው ታሪካዊ ቁርኝት የክለቡን ጥልቅ ህዝባዊና ባህላዊ መሰረት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቀዳሚ ፋና ወጊ የሆነው ይህ ታላቅ ክለብ፣ በታሪካዊቷ የነሐሴ 13 ቀን የቡሄ ዕለት የመስራቾቹ የ"ሆያ ሆዬ" ጨዋታና ከተሰበሰበው ሙልሙል ዳቦ ሽያጭ ባገኟት ሁለት ጠገራ ብር የመጀመሪያውን ቡኒና ነጭ ማሊያ መግዛቱ፣ ክለቡ ከህዝብ ማህፀን የወጣ የህዝብ ሀብት መሆኑን ያረጋግጣል። ይህ ከባህልና ከትውፊት ጋር የተቆራኘ አስደናቂ አጀማመር፣ ከጊዜ በኋላ በ1928 ዓ.ም. ለይፋዊ ምስረታው በር ከፋች ከመሆኑም በላይ፣ በታሪካዊው የመጀመሪያ ጨዋታ ላይ እንደ ይድነቃቸው ተሰማ ያሉ የአፍሪካ እግር ኳስ ታላላቅ መሪዎችና ድንቅ ተሰጥኦዎች እንዲፈጠሩ መሰረት የጣለ የኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ነው።
ትንታኔዎች
የስንዴ አብዮት፦ የኢትዮጵያ ማንሰራራት አብነት
Sep 6, 2026 409
ኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ፍላጎቷ ከ107 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ነው። ይህንን ፍላጎት ለማሟላት ለዓመታት ከ700 ሚሊዮን ዶላር እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ውድ የውጭ ምንዛሬ ለስንዴ ግዢ ስታወጣ ቆይታለች። ከዚህ ቀደም ሀገሪቱ ከዓመታዊ ፍላጎቷ መሸፈን የምትችለው ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ብቻ ሲሆን፣ ቀሪውን በውጭ ግዢ ትሸፍን ነበር። በተለይም የዩክሬንና የሩሲያ ጦርነት በዓለም አቀፍ ደረጃ 30 በመቶ የሚሆነውን የስንዴ አቅርቦት በማወኩ ኢትዮጵያ ከባድ የአቅርቦት ፈተና ውስጥ እንድትገባ አድርጓት ነበር። ይህንን የረጅም ጊዜ ተግዳሮት በዘላቂነት ለመቅረፍ መንግሥት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በስፋት በመተግበር፣አሲዳማ መሬቶችን በኖራ በማከም እና ረግረጋማ ቦታዎችን በቴክኖሎጂ በማድረቅ ታሪካዊ ለውጥ ለማምጣት እርምጃዎችን ወስዷል። በኩታ ገጠም እርሻና በዘመናዊ ማሽነሪዎች አጠቃቀም የታጀበው ይህ የልማት አብዮት ፍሬ አፍርቶ፣ ኢትዮጵያ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ከውጭ የምታስገባውን የንግድ ስንዴ ሙሉ በሙሉ አቁማለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስንዴ ልማት የተመዘገበው ስኬት ከውጭ ማስገባትን ማቆም ላይ ብቻ ሳይወሰን፣ ሀገሪቱ ወደ ውጭ መላክ (ኤክስፖርት ማድረግ) የሚያስችል አቅም እንዳላት ያሳየ መሆኑን አመልክተዋል። በዚህም መሠረት የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን በይፋ የስንዴ ኤክስፖርት የተጀመረ ሲሆን፣ ለዚህ ስኬታማነት የተለያዩ ክልሎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ብሔራዊ የማክሮ ኢኮኖሚና የኤክስፖርት ኮሚቴ ሀገሪቱ የሀገር ውስጥ ፍጆታዋን ሸፍና 32 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም እንዳላት አረጋግጦ፣የ2.9 ሚሊዮን ኩንታል የውል ስምምነቶች ከረድኤትና ከሀገር ውስጥ ድርጅቶች ጋር ተፈራርሟል። ከሀገር ውስጥ አቅርቦት ባሻገር ኢትዮጵያ በ2015 ዓ.ም ለኬንያ ስንዴ ለመላክ ስምምነት የፈረመች ሲሆን፣ ጅቡቲም ከኢትዮጵያ ስንዴ መግዛት እንደምትፈልግ ገልጻ ከኢትዮጵያ የስንዴ ልማት ብዙ ተሞክሮ እንደምትወስድ አመላክታለች። የአፍሪካ ልማት ባንክ ስንዴ ከውጭ እንደማታስገባ እና ምርቷን ለጎረቤት ሀገራት ማስተላለፍ መጀመሯን በማድነቅ ለአህጉሪቱ እንደ ትልቅ የዕድገት ተሞክሮ አቅርቧል። የአሜሪካ የውጭ ግብርና ቢሮ ሪፖርቶችም በኢትዮጵያ የስንዴ ምርት ዘርፍ ትልቅ እመርታ እያሳየ መምጣቱን ጠቅሰው፣መንግሥት የመስኖ ልማትና የግብርና ኤክስቴንሽን ድጋፍ በማጠናከሩ ሀገሪቱ ከፍተኛ ምርት ማምረቷን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ምርት ከ290 እስከ 340 ሚሊዮን ኩንታል (ከ29 እስከ 34 ሚሊዮን ቶን) በላይ መድረሱ ኢትዮጵያን በአፍሪካ አህጉር ቀዳሚ የስንዴ አምራች ሀገር አድርጓታል። የስንዴ ልማቱ አርሶ አደሩን ከቀድሞው ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ አላቆ፣ በኩታ ገጠም እርሻና በሜካናይዜሽን ታግዞ ወደ ሰፋፊ የንግድ ምርት እንዲገባ አስችሏል። የተሻሻሉ የስንዴ የሰብል ዝርያዎች መለቀቃቸው ለዚህ ውጤት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ የምርት አቅርቦት ሰንሰለቱን ማዘመን በቀጣይነት በትኩረት እየተሠራበት ይገኛል። በምርት አቅም እና በኩታ ገጠም እርሻ የተመዘገቡት እነዚህ ሰፊ ስኬቶች፣ ሀገሪቱ በኢኮኖሚ አቅም እያደረገችው ያለውን ሁለገብ ማንሰራራት በግልጽ የሚያሳዩ አብነቶች ናቸው። ይህ ትልቅ ለውጥ ኢትዮጵያ ከድህነትና ከዕርዳታ ጥገኝነት ወጥታ የምግብ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ ለሌሎች አፍሪካ ሀገራትም ተስፋ የሚሰጥ አህጉራዊ አርዓያ መሆን መቻሏን አስመስክሯል። ይህ የምርት እመርታ በግብርናው ብቻ ሳይሆን፣ አጠቃላይ የሀገሪቱን ማንሰራራት የሚያረጋግጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው። ለዘመናት በውጭ ዕርዳታና በለጋሾች ላይ ተወሰና የነበረችው ኢትዮጵያ፣ዛሬ በራሷ አቅም በመሥራት አህጉራዊ አርዓያ መሆን መቻሏ ትልቅ ስኬት ነው። የኢኮኖሚ ነፃነት እና የሉዓላዊነት ማዕቀፍን በማረጋገጥ ረገድም የስንዴ አብዮቱ የሀገርን አቅም የሚያሳይ ተምሳሌት ሆኗል። በመሆኑም በስንዴ ልማት የተገኘው ይህ ድል የግብርና ዘርፍ ስኬት ብቻ አይደለም፤ ኢትዮጵያውያን በቁርጠኝነትና በትጋት ከሠሩ ሀገርን ማሻገር እንደሚችሉ በተግባር ያረጋገጡበት ታላቅ የሀገር የማንሰራራት ማሳያ ነው።
የቡና ወጪ ንግድ እድገት - የኢትዮጵያ እመርታ አንዱ ማሳያ
Sep 5, 2026 314
ገና ወደ ውስጥ ሲገቡ ለምለም ቄጠማ በተጎዘጎዘበት ቤት እና ትኩስ በተቆላ ቡና ከደማቅ ፈገግታ ጋር አቀባበል ታደርጋለች። የቡናው ሽታ ደግሞ ልዩ መዐዛ አለው። አለምነሽ ሀብቱ ወደ ከተማ ከገባች በኋላ ድሮም የምትወደውን ቡና የሰርክ ስራዋ የእለት መተዳደሪያዋ አድርጋዋለች። ቡና ትወዳለች የአዘገጃጀት ድምቀቷንም ሌሎች ይወዱላታል። እሷ የምታዘጋጀውን የጀበና ቡና ለመጠጣት የመጣ ደንበኛዋ አትርፎ እንደወጣ እንዲሰማው የማድረግ ተሰጥኦ አላት። ቡና ትወዳለች ትጠጣለች ታጠጣለች ። እንደሷ ሁሉ ቡና ለኛ ለኢትዮጵያውያን አብሮን የሚውል፣ የሚያመሽ በብዙዎቻችን ቤት በቋሚነት የማይጠፋ ማህበራዊ መገናኛችን መመካከሪያችንም ጭምር ነው። በቡና ምርት በርካታ መሬትን ሸፍና ብዙ አርሶ አደሮችን እያሳተፈች የወጪ ንግዷን ለማሳደግ የምትጥረው ኢትዮጵያ ደግሞ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የምታገኝበት ዋንኛ የግብርና ኢኮኖሚው የጀርባ አጥንትም ነው። ባለፉት ዓመታት የቡና ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ ድርሻም እያሳደገ መምጣቱን የተለያዩ መረጃዎች እያሳዩ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄ ማብራሪያ ሲሰጡ ለቡና ልማት የተሰጠው ትኩረት ኢትዮጵያን በአለም ሶስተኛዋ ቡና ላኪ ሀገር እንድትሆን ማስቻሉን ማንሳታቸው ይታወሳል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም ከቡና ወጪ ንግድ የተገኘው ከ3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ወደ ውጭ ከላከቻቸው ምርቶች ከፍተኛው እንደነበረም አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከብራዚልና ከኮሎምቢያ በመቀጠል በዓለም 3ኛዋ ትልቋ የቡና ላኪ ሀገር መሆኗን እና በአፍሪካም ቀዳሚ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን የሀገር ውስጥ የቡና ፍጆታ ከመቻል አልፈን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የመጣው ለውጥ የሀገራዊ የሪፎርሙ ስኬት መገለጫ ነው ማለታቸውም ይታወሳል። ይህ የአንድ ዓመት ምርት እንግዲህ ኢትዮጵያ ባለፉት 17 አመታት ቡናን ወደ ውጭ በመላክ ካገኘችው 3 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ጠቅላላ ገቢ ጋር ሲነጻጸር አስደማሚ ስኬት መሆኑ አያጠራጥርም። አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለቡና ኤክስፖርት እድገት ስኬት አስተዋጽኦ ማበርከቱን በወቅቱ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቡናን ካልተከልን ፤ ካልተንከባከብን ፤ካልለቀምን፤ ካላጠብን፤ካላሸግንና ካላጓጓዝን ይህ ውጤት ሊመጣ አይችልም ብለውም ነበር። ኢትዮጵያ የአረቢካ ቡና መገኛ እንደመሆኗ የምርቱን እድገትና ዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ተፈላጊነቱን ለማሳደግ እየተከናወኑ ባሉ ተከታታይ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል። ባለፉት ተከታታይ ዓመታት የተከናወነ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በሌሎች ኢኮኖሚያዊ፣ አካባቢያዊና የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳራዊ ግዙፍ አበርክቶው እንዳለ ሆኖ በቡና ምርት እድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ለዚህ ማሳያው ደግሞ መርሃ-ግብሩ ሲጀመር በ2011 ዓ.ም. ስድስት መቶ ሺህ ችግኝ የተተከለ ሲሆን ዓመታዊ ምርቱም 5 መቶ ሺህ ሜትሪክ ቶን ነበረ። በወቅቱ የተገኘው የውጭ ምንዛሪም 738 ሚሊዮን ዶላር ነበር። ይሄ ትኩረት በመቀጠሉም የቡና ችግኝ የመትከሉ ስራ አድጎ በ2017 ዓ.ም. ላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን በዛው ዓመት 2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ተችሏል። ከላይ እንደተገለጸው የ2018 የቡና ወጪ ንግድ ገቢ 3 ነጥብ 1 መድረሱ ለዘርፉ የተሰጠውን ትኩረት እና የተመዘገበውን እመርታ የሚያሳይ ነው። ለዓመታት በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የቆየው የቡና ወጪ ንግድ ገቢ በአጭር ጊዜ መለወጥ እና ኢትዮጵያ ወደ ተለያዩ ሃገራት ከምትልካቸው የግብርና ምርቶች ከፍተኛውን ድርሻ ይዞ መቀጠሉ ለዘርፉ ለተሰጠው ትኩረት እና ለተገኘው ውጤት አንዱ መገለጫም ነው። የኢትዮጵያ ቡና በዓለም ገበያ ላይ ተፈላጊነቱ በየጊዜው እየጨመረም ይገኛል። ጀርመን፣ አሜሪካ፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ጃፓን፣ ቤልጂየም እና ደቡብ ኮሪያ ከቀዳሚዎቹ የኢትዮጵያ ቡና ገዢዎች መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን በቻይና እና በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የቡና ፍጆታና የመጠጣት ባህል በፍጥነት ማደጉ ለኢትዮጵያ አዳዲስ የገበያ እድሎችን ፈጥሯል። ይህ የኢትዮጵያ የእመርታ ጉዞ በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል ብልጽግናዋንም የምታረጋግጥ የዳበረ ኢኮኖሚ ያላትና የበለጠ ጠንካራ ሀገርነቷን የምታስቀጥልበት አዲስ ምዕራፍም ነው።
ለኢትዮጵያ የቤት ልማት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ስምምነት
Sep 4, 2026 315
የኢትዮጵያ የከተሞች ዕድገት ፈጣን እየሆነ በመምጣቱ እና የሕዝብ ቁጥር ዕድገት ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ በመሄዱ፣የዜጎችን የቤት ባለቤትነትን ጥያቄ በዘላቂነት መመለስ የመንግሥት አንዱ ዋና የትኩረት አቅጣጫ ሆኗል። ባለፉት ዓመታት የነበረው የቤት አቅርቦት በመንግሥት ትከሻ ላይ ብቻ የወደቀ በመሆኑ፣ ካለው ሰፊ የሕዝብ ፍላጎት ጋር አብሮ ለመሄድ ፈታኝ ሆኖ ቆይቷል። ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት መንግሥት አዲስ የቤት ልማት ፖሊሲ ቀርጾ በካቢኔ ማጽደቁ ይታወቃል። ፖሊሲው የዕድገቱን ፍጥነት እና የከተሞችን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ ነው። በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እየተከናወኑ ያሉ የኮንስትራክሽንና የከተማ ልማት ሥራዎች ለዚህ ሰፊ ራዕይ ግልጽ ማሳያዎች ናቸው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ በመላ ሀገሪቱ 1.2 ሚሊዮን ቤቶችን መገንባት መቻሉን አስታውሰዋል።   ይህንኑ ስኬት መሠረት በማድረግ፣ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን አዳዲስ ተመጣጣኝ መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት መንግሥት አጠቃላይ ዝግጅት አድርጎ እየሠራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። አሁን ላይ አዲስ የግንባታ ቴክኖሎጂንና የረጅም ጊዜ የቤት ብድር ሥርዓትን በማስተዋወቅ የዜጎችን የቤት ባለቤትነት ጥያቄ በዘላቂነት ለመመለስ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል። አዲሱ የቤት ልማት ፖሊሲ ተቀርጾ በካቢኔ መጽደቁንና በሁሉም ክልሎች የተቀናጀ ንቅናቄ መጀመሩን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ግንባታው በመንግሥት በጀት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን፣ የግሉ ዘርፍ እንዲሁም የመንግሥትና የግል አጋርነት መዋቅሮችን በስፋት መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የዜጎችን የመግዛት አቅም ያገናዘበና ፍላጎታቸውን የሚያስተናግድ አዲስ የፋይናንስ አሠራር መፈጠሩን ጠቅሰው፤ሰዎች ቤት በቀጥታ መግዛት ካልቻሉ በመንግሥት በሚመቻቸው አዲስ የሞርጌጅ ሥርዓት አማካኝነት ከገቢያቸው ላይ እየከፈሉ በረጅም ጊዜ ሂደት የቤት ባለቤት የሚሆኑበት ዕድል ይፈጠራል ብለዋል። ይህ ግብ የዜጎችን የቤት ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ የግሉን ዘርፍ በስፋት በማሳተፍ የሚሳካ መሆኑ በግልጽ ተቀምጧል። የሞርጌጅ ሥርዓት የቤት ፍላጎትን ለማሟላት የቀረበ ሌላኛው አማራጭ ሆኗል። የቤት መግዣ ብድር ሥርዓት (ሞርጌጅ) ማለት አንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ለመግዛት የሚያስፈልገውን ገንዘብ ከባንክ በብድር አግኝቶ፣ ያንን የተበደረውን ገንዘብ ከነወለዱ በረጅም ዓመታት መልሶ የሚከፍልበት የፋይናንስ አሠራር ነው። ይህ አሠራር አቅማቸው ውስን ለሆኑ ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በወር በወር እየከፈሉ የቤት ባለቤት የመሆን ልዩ ዕድል ይፈጥራል። የከፍተኛ የቤት ኪራይ ወጪን በማስቀረት ዜጎች በየወሩ የሚከፍሉት ገንዘብ በራሳቸው ንብረት ላይ የሚደረግ ጠቃሚ ኢንቨስትመንት እንዲሆን ያደርጋል። ይህንን ታላቅ ራዕይ ከግብ ለማድረስ በዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መካከል በሀገሪቱ የመጀመሪያው የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ተፈጽሟል። በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅዖ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፉ ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው ገልጸዋል። ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት የተቀመጠውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን እንደምትቀጥልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።   የዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ማክታር ዲዮፕ በሰጡት አስተያየት፣ ይህ አጋርነት በኢትዮጵያ የከተሞች ልማት ላይ የግል ባለሀብቶች በስፋት እንዲሳተፉ ትልቅ ምቹ ምህዳር እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ጠንካራ የቤት ፋይናንስ ገበያ የዜጎችን ሕይወት ለማሻሻል እና የኢኮኖሚ ዕድገትን ለመደገፍ ቁልፍ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዳዩ እንዲጀመር እንዲሁም ሂደቱ ላይ ክትትል በማድረግ እያከናወኑት ላለው ሥራና አመራር ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በዚህ የፋይናንስ ማዕቀፍ አማካኝነት ዜጎች ሙሉ የቤት መግዣ ገንዘብ እስኪኖራቸው ሳይጠብቁ በባንክ ብድር የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ይደረጋል።ግንባታው በመንግሥት በጀት ብቻ ሳይሆን በመንግሥት፣ በግል ዘርፍ፣ እንዲሁም በመንግሥትና በግል አጋርነት (PPP) ይከናወናል። የሞርጌጅ ፋይናንስ ሥርዓቱ የዜጎችን ማህበራዊ ዋስትና በማረጋገጥ የባለቤትነት ስሜት ከመፍጠር አኳያ ያለው ፋይዳ ቁልፍ የሚባል ነው። መንግሥት ብቻውን ሊያከናውነው የሚችለውን ግዙፍ የልማት ጫና፣የግሉን ዘርፍ እና ዓለም አቀፍ አጋሮችን በማስተባበር በጋራ መወጣት እንደሚቻል የዛሬው ስምምነት ግልጽ ማሳያ ነው። የ100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ፈንድ እና የ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ዕቅድ እውን መሆን፣ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ጉዞ የሚያፋጥንና ሁሉንም ዜጎች አካታች የልማት ባለቤት የሚያደርግ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
የኮሪደር ልማት እና የነገዋ ኢትዮጵያ
Sep 4, 2026 226
በኢትዮጵያ አሁን ላይ በተለያዩ መስኮች እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች መጻኢውን ጊዜ ብሩህ ለማድረግ መሰረት የሚጥሉ ናቸው። ከእነዚህ ስራዎች በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው የሀገሪቱን ከተሞች ገጽታና የነዋሪዎቿን የኑሮ ዘይቤ በከፍተኛ ደረጃ እየቀየረ ያለው የኮሪደር ልማት መርሃ ግብር ነው። ይህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የኮሪደር ልማት ከተሞችን ለኑሮ ምቹ፣ ንጹህና ስልጡን በማድረግ ትልቅ ምዕራፍ ከፍቷል። በአጭር ጊዜ ውስጥ ያስመዘገበው ስኬትና የፈጠረው አርአያነት አሁን ላይ አዲስ አበባን አልፎ በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች ተግባራዊ ተደርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ የኮሪደር ልማት ከከተማ ውበትና ገጽታ ባለፈ የሀገሪቱን የዕድገት አቅጣጫ በከፍተኛ ደረጃ እየቀየረ ያለ እና የነገዋን ሀገር ዛሬ ላይ የመቅረጽ ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው። በኮሪደር ልማቱ ለእግረኛ እና ለአካል ጉዳተኞች ፈታኝ የነበሩ መንገዶች ዛሬ ሰፊና ጥራት ባላቸው የኮንክሪት ንጣፎችና የብስክሌት መስመሮች ተተክተዋል።   በከተሞች የሚገኙ የመዝናኛ ፓርኮች፣ የማረፊያ ስፍራዎች እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ ቦታዎች የዜጎችን ማኅበራዊና ሰብአዊ ክብር ከፍ ያደረጉ ሲሆን፤ እነዚህ ጥራት ያላቸው መሠረተ-ልማቶች የነገውን ጤናማ እና ማህበራዊ ፍትሕ የሰፈነበት ማህበረሰብ ለመፍጠር የተጣሉ ጠንካራ መሠረቶች ናቸው። የኮሪደር ልማት የከተሞችን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ወደ ዘመናዊነት በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በዘመናዊ የጎዳና ላይ መብራቶችና የደህንነት ካሜራዎች የታገዙ ከተሞች በቀን ብቻ ሳይሆን በሌሊትም የንግድና የኢኮኖሚ ማዕከል እንዲሆኑ በር በመክፈታቸው፣ የ24 ሰዓት የስራ ባህልን በመፍጠር ለአያሌ ወጣቶችና አነስተኛ ነጋዴዎች አዲስ የሥራ ዕድል ፈጥረዋል። በሌላ በኩል፣ ይህ ስትራቴጂካዊ ልማት ኢትዮጵያን ወደ ቋሚ የኮንፈረንስ፣ የንግድ እና የባህል ቱሪዝም መዳረሻነት እየቀየራትም ይገኛል። በተለይም የከተሞችን ማህበራዊ መስተጋብርና የሕዝቡን አንድነት በማጠናከር ረገድ የኮሪደር ልማቱ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ ነው። በልማቱ የተፈጠረው የጋራ ትስስር የነገዋን ጠንካራ፣ ሰላማዊና በአብሮነት የታነጸች ሀገር ለመገንባት እንደ ትልቅ ማህበራዊ መሰረት ያገለግላል። የነገዋ ኢትዮጵያ በዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም ያደገችና አሰራሯ የዘመነ መሆኑን የሚያረጋግጥ ተግባራዊ እርምጃ ከኮሪደር ልማቱ ጋር ተሳስሮ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል።   ስራው ከቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በቅንጅት በማከናወን ዘመናዊ የትራፊክ ቁጥጥር ሥርዓቶች እና የስማርት ከተማ መተግበሪያዎች መሰረተ ልማት አብሮ እየተዘረጋ ይገኛል። በተጨማሪም ከኮሪደር ልማት ጋር እየተከናወነ ያለው መጠነ ሰፊ የአረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዞች ዳርቻ ልማቶች ከተሞች ከአየር ንብረት ለውጥ ስጋትና ሙቀት በመከላከል ለትውልዱ ንጹህና ጽዱ መኖሪያን አካባቢን ለማስረከብና ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት እያስቻለ ነው። በአጠቃላይ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከአንድ ከተማ ገጽታ ማሻሻል ባሻገር፣ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ በርካታ ክልል ከተሞች ላይ በመስፋፋት ሀገራዊ ለውጥ ፈጥሯል ማለት ያስችላል። የዚህ ዘርፈ ብዙ የልማት ፍሬ ዛሬ ላይ የኑሮ ዘይቤን እያሻሻለ እንደሚገኘው ሁሉ፣ ለወደፊቱ ትውልድም የኩራት ምንጭ የሆነ ዘላቂ ሀብት ሆኖ ይሸጋገራል። ዛሬ በጥራትና ውብ ሆነው እየተሰሩ ያሉ መንገዶች፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ የህጻናት መጫወቻ ስፍራዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች እና የዲጂታል መሰረተ ልማቶች የነገዋ ኢትዮጵያ የበለጸገች፣ ስልጡንና ለኑሮ ምቹ የማድረግ ራዕይን እውን የሚያደርጉ ናቸው።
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 12813
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 22209
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 15242
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20982
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 106041
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 80302
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 58641
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 56247
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 40121
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 40036
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 39494
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 37978
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 106041
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 80302
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 58641
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 56247
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ የማዕድን ምርት እመርታ
Aug 21, 2026 1136
በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአገር በቀል የኢኮኖሚና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ታግዞ፣ ባለፉት ዓመታት የታዩበትን የአሰራርና መዋቅራዊ ችግሮች በመቅረፍ ከፍተኛ የመነቃቃት ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ዘርፉ በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ ማዕድን በብዝኃ ዘርፍ የልማት ምልከታችን ውስጥ እና በሀገሪቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል። ባለፉት ሶስት አሥርት ዓመታት ውስጥ የማዕድን ዘርፉ ለአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ያበረከተው አስተዋጽኦ ከ0 ነጥብ 8 በመቶ በታች የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ግን መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው የላቀ ትኩረት ከፍተኛ መዋቅራዊ ሽግግር እያመጣ ይገኛል። በ2018 በጀት ዓመት ከዘርፉ 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ተችሏል። ይህም ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ92 በመቶ የገቢ ዕድገትና የ27 በመቶ የምርት መጠን ብልጫ ያሳየ ሲሆን፣ ምርቶቹም በዋናነት ወደ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ አሜሪካ፣ ጀርመን እና ቻይና ተልከዋል። በወጪ ንግድ እድገት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው የወርቅ ምርት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት 22 ነጥብ 5 ቶን ለውጭ ገበያ የቀረበ ሲሆን እስከ ዓመቱ ማብቂያ 32 ቶን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።   በባህላዊ መንገድ የሚመረተውን የወርቅ ምርት ለማዘመንም መንግሥት የማጣሪያና ማቀለጫ ፋብሪካዎችን በመገንባት ላይ ይገኛል። የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ከውጭ የሚገቡ ስትራቴጂክ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህም ለድንጋይ ከሰል ግዢ ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ ማስቀረት የተቻለ ሲሆን፣ የሲሚንቶ ምርትም ባለፉት ስምንት ዓመታት ከነበረበት 8 ሚሊየን ቶን አሁን ላይ በዓመት ወደ 14 ሚሊየን ቶን አድጓል። ሀገሪቱ በየዓመቱ ለማዳበሪያ ግዢ የምታወጣውን 2 ቢሊየን ዶላር ለማስቀረትም የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ተጀምሯል። በተጨማሪም በየዓመቱ ለብረት ምርት ግዢ የሚወጣውን 1 ቢሊየን ዶላር በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት የሚያስችል ግዙፍ ፋብሪካ የመገንባት ስምምነት ተፈጽሞ ወደ ስራ ተገብቷል። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በዘርፉ የተሰማሩ ፕሮጀክቶች ዋጋ 10 ቢሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ከለውጡ በፊት ከነበረውና ከ100 ሚሊየን ዶላር የማይበልጡ አነስተኛ ኢንቨስትመንቶች በከፍተኛ ደረጃ የለወጠ ስኬት ነው። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በአፋር ክልል የሚገኘውን ግዙፍ የፖታሽ ክምችት ለማልማት ፈቃድ አግኝቶ ወደ ሥራ ገብቷል። በተጨማሪም ታንታለምን እሴት ጨምሮ ለመላክ ከአሜሪካ ኩባንያ ጋር ድርድር እየተደረገ ሲሆን፣ ለባትሪና ቴክኖሎጂ ወሳኝ የሆኑትን ሊቲየም፣ ኮባልትና ኒኬልን ለማምረት ዝግጅት ተጠናቋል። የኢንቨስትመንት ምህዳሩን ሳቢ ለማድረግ የማዕድን ፈቃድ አሰጣጥ አሰራር ቅድሚያ የመጣን ቅድሚያ ማስተናገድ በሚል መርህ እንዲመራ ተደርጓል። የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና መላኪያ ፈቃዶች፣ እንዲሁም የካዳስተር ሲስተም ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ኤሌክትሮኒክስ አሰራር ተሸጋግረዋል። በ2019 በጀት ዓመት ከዘርፉ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፣ የመንግሥት ስትራቴጂካዊ እቅድ እ.አ.አ. በ2030 የማዕድን ወጪ ንግድ ገቢን ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ በማድረስ ኢትዮጵያን ከአፍሪካ አምስት ቀዳሚ የማዕድን አምራች ሀገራት ተርታ ማሰለፍ ነው።   በዘርፉ እየተካሄደ ያለው መዋቅራዊ ሽግግር ኢትዮጵያ በውጭ ምርቶች ላይ ያላትን ጥገኝነት በመቀነስ ወደ ኢንዱስትሪ መሪነት የምታደርገውን ጉዞ ያፋጥነዋል። የወርቅ፣ የተፈጥሮ ጋዝ፣ የፖታሽ እና የቴክኖሎጂ ማዕድናት በሀገር ውስጥ እሴት ተጨምሮባቸው ለዓለም ገበያ መቅረባቸው ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ላይ የሚኖራትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ያረጋግጣል።
የአረቡ ዓለም ከግብፅ ምን አተረፈ?
Aug 19, 2026 909
የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ አካሄድ በታሪካዊ እውነታዎች እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ላይ እየተመሠረተ በመጣበት በአሁኑ ወቅት፣ ጊዜ ያለፈባቸው የጂኦ ፖለቲካዊ የመጠላለፍ አካሄዶች ዋጋ ቢስነትና ጥቅም አልባነት በግልጽ እየታየ ይገኛል። ለብዙ አስርት ዓመታት ግብፅ የዓረብ ሊግን ለራሷ ጠባብ ፍላጎቶች እና ጂኦፖለቲካዊ አጀንዳዎች ማስፈጸሚያነት በሰፊው ስትጠቀምበት ቆይታለች። ሆኖም ይህ ጥቅምና ጉዳትን ብቻ መሰረት ያደረገ ግንኙነት አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ያስነሳል፦ ለመሆኑ የዓረቡ ዓለም ከግብፅ በምላሹ ያገኘው ትርፍ ምንድን ነው? ለዚህ ጥያቄ አጭሩ መልስ ምንም የሚል ነው ሲል “What Has the Arab World Gained from Egypt? Why Ethiopia Belongs in the Arab League?” ፀሐፊው እና በፖለቲካና ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ በቋሚነት የሚተነትነው አስተያየት የሚሰጠው ጅብሪል ላሞ በኢዜአ እንግሊዘኛ ገጽ ባሳፈረው ሐተታ ላይ ፣ የግብጽ ፖሊሲዎች እንዲሁም ለሁለት አስርት ዓመታት የዘለቀው አምባገነናዊ አስተዳደር የጋራ ጥንካሬን ከመፍጠር ይልቅ የቀጣናውን አለመረጋጋት ማባባሳቸውን ገልጿል። እነዚህ ፖሊሲዎች፣ በምሥራቅ አፍሪካ እና በቀይ ባሕር አካባቢም ውጥረትን እያባባሱ እንደሚገኙ አመልክቷል። እነዚህ አካባቢዎች ለዓረቡ ዓለም የራቁ አይደሉም፤ ይልቁንም ለዓረቡ ዓለም ደኅንነት፣ የባሕር ንግድ፣ የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የምግብ ዋስትና እጅግ ወሳኝ እና ስትራቴጂካዊ ማዕከላት ናቸው። የግብፅ ከፋፋይ ቀጣናዊ አካሄድ ከታዩባቸው ጉልህ ማሳያዎች አንዱ በኤርትራ ጉዳይ እና በሰፊው የኢትዮጵያ ግዛት አንድነት ላይ የነበራት ታሪካዊ ጣልቃ ገብነት ነው። ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ቀጣናዊ ተፅዕኖዋን ለመግታት በግብጽ ታስበው የተደራጁ ተገንጣይ ኃይሎችን እና ፖለቲካዊ ፕሮጀክቶችን በግልጽ ትደግፍ እንደነበረ ፀሐፊው አውስቷል። ከኢትዮጵያ የኤርትራ መገንጠል በምሥራቅ አፍሪካ ቀውስ የተሞላ ታሪክ ውስጥ አቢይ ክስተት ሲሆን፣ የውጭ ጂኦፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነቶች የሀገራትን እጣ ፈንታ እንዴት እንደሚያናጉ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የዲፕሎማሲ ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ የቀድሞው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ እና የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ቡትሮስ ቡትሮስ-ጋሊ፣ ኢትዮጵያን ለማዳከም ታስቦ የተዘረጋውን የኤርትራን የመገንጠል ፕሮጀክት በመደገፍና በማፋጠን ረገድ ትልቅ ሚና ነበራቸው። በተጨማሪም ግብጽ በደቡባዊ የቀይ ባህር ቀጣና የምታካሂደው ቀውስ የመፍጠር እንቅስቃሴ፣ ለዓለም አቀፍ የባህር ንግድና ለቀጣናው ደህንነት ቀጥተኛ ስጋት ደቅኗል። በባብ-ኤል-ማንደብ የባሕር ወሽመጥ አካባቢ ውጥረቶችን በመቀስቀስ እና ተላላኪ ታጣቂ ቡድኖችን በማንቀሳቀስ፣ ወሳኝ የሆኑ የባህር መተላለፊያዎችን የጂኦፖለቲካዊ ግጭት መድረክ አድርጋዋለች። ይህም ለጠቅላላው የዓረብ ዓለም የኢነርጂና የምግብ አቅርቦት መሰረት የሆነውን የደህንነት መዋቅር አደጋ ላይ ጥሎታል፤ ሲሉ ጅብሪል ላሞ ያብራራሉ። ጅብሪል ላሞ በጽሑፉ ላይ እንዳሰፈረው፣ የግብፅ ግልጽ የራስ ወዳድነት እንቅስቃሴዎች ቀጣናዊ ውጥረትን የሚፈጥሩ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ መቀላቀል ግን ለዓረቡ ዓለም እጅግ ከፍተኛ ጥቅም የሚያስገኝ ለውጥ አምጪ ዕድል ይዞ ይመጣል። በመደመር ፍልስፍና አሳታፊ ማዕቀፍ ሥር፣ ኢትዮጵያ ከማግለል ፖሊሲ ይልቅ የዓረቡን ዓለም ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማስተሳሰር የሚያስችል የላቀ የዲፕሎማሲ አቅም አላት። በዚህም የአፍሪካ ዋነኛ የዲፕሎማሲ ማዕከል እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ የባለብዙ ወገን ትብብሮችን በመቅረጽ ረገድ ያላትን የካበተ ልምድ ታካፍላለች። የኢትዮጵያ ወደ ዓረብ ሊግ የመቀላቀል ጥረት ጊዜያዊ የፖለቲካ ስሌት ሳይሆን፣ የተፈጥሮ የታሪክ ጥሪ ነው። ከ135 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ፣ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እና ጥልቅ የሥልጣኔ መሠረት ያላት ይህች የቀይ ባሕር ሀገር፣ አባልነቷ በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቅ መካከል ስትራቴጂካዊ ድልድይ ይፈጥራል። ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር ያላት ቁርኝት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በጋራ ታሪክ፣ ባህል እና የደም ትስስር ላይ የተገነባ ነው። እንደ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባሉ የትምህርት ተቋማት፣ የኢትዮጵያ ጥናቶች በታሪክ ደረጃ ከመካከለኛው እና ከቅርብ ምሥራቅ ታሪክ (Near Eastern Studies) ተመድቦ መጠናቱ፤ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ከቀጣናው ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ ውህደት የሚያረጋግጥ ሕያው ማሳያ ነው። የባብ-ኤል-ማንደብ የባህር ወሽመጥ በጭራሽ መሰናክል አልነበረም፤ ይልቁንም ንግድን፣ ባህልን እና ማህበረሰቦችን በቀይ ባሕር በኩል ያገናኘ ዋንኛ መተላለፊያ ሆኖ አገልግሏል። ከንጉሥ አብረሃ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ በኢትዮጵያውያን እና በመካከለኛው ምሥራቅ ሕዝቦች መካከል የጋራ የደም ትስስር እንደነበር የሚያረጋግጡ ዘመናዊ የስነ ህይወት( ጄኔቲክስ) ጥናቶች፣ የዚህን ታሪካዊ ቁርኝት እውነተኛነት በግልጽ ያሳያሉ። በቋንቋና በባህል ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት መሠረት ታሪካዊ ትስስር ያለው ነው። የሀገሪቱ የቋንቋና የሥነ-ጽሑፍ ውርስ ከዓረብኛ፣ አራማይክና ዕብራይስጥ ጋር በጽኑ የተሳሰረ ሲሆን፣ ይህም በምሥራቅ አፍሪካና በአረቢያ ልሳነ-ምድር መካከል ያለውን ጥልቅ የጋራ የሥልጣኔ ቁርኝት ያረጋግጣል። ኢትዮጵያ በእስልምና ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ አላት። የመጀመሪያዎቹ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ተስደው በንጉስ ነጃሺ ከለላ ማግኘታቸው የእስልምናን ህልውና የታደገ ታሪካዊ ክስተት ሲሆን፣ ይህም ሀገሪቱን ከዓረቡ ዓለም ጋር በጽኑ አስተሳስሯታል። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ የዓረብ ሊግን በኢትዮጵያ ላይ እንደ ተቋማዊ ተፅዕኖ ማሳደሪያ መሣሪያ ግብጽ ስትጠቀምበት ቆይታለች። ግብፅ የውጭ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ዕድገት፣ የህዳሴውን ግድብም ሆነ የባሕር በር ጥያቄን እንደ ሥጋት በሚያይ ጊዜ ያለፈበት ስሌት ላይ የተመሠረተ ነው። ግብፅ የራሷን የውሃ አቋም በሊጉ ላይ በመጫን፣ ተቋሙ ከኢትዮጵያ ጋር አላስፈላጊ ውጥረት ውስጥ እንዲገባ አድርጋለች። ጅብሪል ላሞ እንዳመለከተው፣ ከግብጽ የአግላይነት ፖሊሲ ይልቅ የዘመኑ ነባራዊ ሁኔታዎች ሙሉ ትብብርን የሚጠይቁ ናቸው። በመደመር መርህ፣ ኢትዮጵያ ለዓረቡ ዓለም ለዘመናት ከቆዩ የጥላቻ መንገዶች በላቀ ሁኔታ የተሻሉ ጥቅሞችን ማቅረብ ትችላለች። እያደገ የመጣው የኢንዱስትሪ እና የአረንጓዴ ኃይል አቅሟ፣ ኢትዮጵያን ለቀይ ባህር ቀጣና የመረጋጋት ምሰሶ አድርጓታል። የመካከለኛው ምሥራቅ ቀጣና የውሃ እጥረት እና የምግብ ዋስትና ሥጋት በተጋረጠበት በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ የውሃ ሀበት እና ለም መሬት ለቀጣናው ወሳኝ የግብርና-ኢንዱስትሪ አጋር ያደርጋታል። የዓረብ ሊግ አባል ሀገራት የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ብሔረተኝነት በመሻገር፣ የቀይ ባህርን ቀጣና የሥልጣኔ እውነታ መቀበል ይኖርባቸዋል። አረብ ሊግ እንደ ጅቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ኮሞሮስ እና ሞሪታኒያ አባል ሀገራት መያዙ፣ ስብስቡ የተለያዩ ቀጣናዊ እውነታዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑን ያሳያሉ። የዓረብ ሊግ ሙሉ አባልነት የኢትዮጵያን አፍሪካዊ ማንነት ሳይቀንሰው፣ አህጉሩን ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር የሚያገናኝ ዋነኛ ድልድይ የሚያደርጋት በመሆኑ፤ ሊጉ የኢትዮጵያን አጋርነት በመቀበል ለአዲስ አበባ ተገቢውንና ሕጋዊ ቦታዋን የሚሰጥበት ጊዜ አሁን እንደሆነ በመግለጽ ጅብሪል ላሞ ፅሁፉን ቋጭቷል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም