ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የፌዴራል መንግስት በክልሉ እያከናወናቸው የሚገኙ ፕሮጀክቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ ነው- ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ
Dec 10, 2025 53
መቀሌ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል እያከናወናቸው የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ ገለጸ። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ፤ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ የልማት ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ሚኒስቴሩ በመቀሌ ከተማ ዳርቻ ላይ በ2 ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ወጪ ለሚገነባ የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በትግራይ ክልል ከውሃና ሳኒቴሽን ጋር የተያያዙ የልማት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑም ተመላክቷል።   በዚህ ወቅት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ ፤ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል እያከናወናቸው የሚገኙት የልማት ፕሮጀክቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን አረጋግጠዋል። መሰል የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል። በመቀሌ ተገኝተው ለፕሮጀክቱ የመሰረተ ደንጋይ ያስቀመጡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ፤ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል ለማህበራዊ አገልግሎት የሚውሉ የግንባታ ፕሮጀክቶችን ማከናወኑን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ በዛሬው ዕለት በመቀሌ ከተማ ዳርቻ ላይ የሚገነባ የፍሳሽ ማስወገጃና ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምሯል ብለዋል።   ይኸው የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክትም በመቀሌ ከተማ ዳርቻ ላይ በ2 ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ወጪ የሚገነባ መሆኑንም አስታውቀዋል። የከተማው የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክትም በአካባቢው ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች በመስኖ ልማት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅም ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። በክልሉ በአምስት ከተሞች የውሃና ሳኒቴሽን አገልግሎት የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን ሚኒስቴሩ እያከናወነ መሆኑንም አንስተዋል። ሚኒስቴሩና ተጠሪ ተቋማቱ ከዚህ ቀደምም በከተማዋ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ቤቶችን በመገንባት ማስረከባቸው ይታወሳል። በእንደርታ ወረዳ የማይ ዓለም ገጠር ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ቄስ ገብረኪዳን ታደሰ ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ወጣቶች የስራ ዕድል ከመፍጠሩም ባሻገር በመስኖ ልማቱ በመጠቀም ከተረጂነት ለመውጣት የሚደረገውን ጥረት እናግዛለን ብለዋል። ወይዘሮ ለተመሰቀል ሀዱሽ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ ለልጆቻችን ተጨማሪ የሥራ ዕድልን ይፈጥራል ብለን እንጠብቃለን ብለዋል።
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በዲጂታል ክፍያ ያስመዘገበችው አስደናቂ ስኬት ተጨማሪ ግቦችን ለማሳካት መሠረት የሚሆኑ ናቸው
Dec 10, 2025 54
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በዲጂታል ክፍያ ያስመዘገበችው አስደናቂ ስኬት ተጨማሪ ግቦችን ለማሳካት መሠረት የሚሆኑ ናቸው ሲሉ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ። ሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል።   በጉባኤው ማጠናቀቂያ ንግግር ያደረጉት የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል ክፍያ ዘርፍ እያስመዘገበች ያለችው ዕድገት አስደናቂ ነው። አሁን ላይ አብዛኛው ዜጋ ከፍተኛ መጠን ያለው ጥሬ ገንዘብ መያዝ አቁሟል ያሉት ገዥው፤ ኢትዮጵያውያን የዲጂታላይዜሽን እና የዳታ ሽግግርን በፍጥነት እየተላመዱ እንደሚገኙም አስረድተዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በተዘረጋው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በየዓመቱ ከ18 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር መከናወኑን ተናግረዋል። ይህን የገንዘብ ዝውውር በጥሬ ገንዘብ ቢከናወን ከፍተኛ ወጪና መጨናነቅ ይፈጥር እንደነበር ጠቁመው፤ ይህ ስኬት ከጥቂት ዓመታት በፊት ፈጽሞ የማይታሰብ እንደነበር ጠቅሰዋል። የመሠረተ ልማትን ለማስፋፋት የተሰጠው ትኩረት ዋነኛ የስኬቱ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥትን ወደ ዲጂታል ግብይት እና የገንዘብ ዝውውር አገልግሎት ለማሸጋገር የሰጠው ትኩረት ለተመዘገበው ውጤት ትልቅ እርምጃ መሆኑን ጠቅሰው፤ በትክክል የታሰበበት፣ በጥንቃቄ የተቀረጸና ተግባራዊ የተደረገ የስትራቴጂ ውጤት ስለመሆኑም ጠቁመዋል። እስካሁን የተገኘውን ውጤት ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰራ ጠቁመው፤ ውጤቱ የሚያዘናጋ ሳይሆን መስፈንጠሪያ ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል። በቀጣይ የዲጂታል ባንኪንግ ተጠቃሚዎችን እምነት ለማሳደግ እና የሥርዓቱን ደኅንነት ይበልጥ ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ጠቅሰው፤ በገጠርና በከተማ ያለውን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልዩነት ለመቀነስ ይሠራል ብለዋል። እንዲሁም የፈጠራ ሥራዎችን በበቂ ሀብት የመደገፍ ሥራዎች ወሳኝ በመሆናቸው በልዩ ትኩረት ይሠራል ብለዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በቁርጠኝነት ሠርታ ያስመዘገበቻቸው ትላልቅ ውጤቶች በቀጣዮቹ ዓመታት ለማሳካት ያስቀመጠቻቸውን ግቦች ለማሳካት ትልቅ መሠረት የሚሆኑ ናቸውም ብለዋል። ኢትዮጵያ የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን ለመገንባት ትክክለኛ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመቅረፅ ትክክለኛውን እርምጃ መውሰዷንም ገልጸዋል። ሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ የመረጃ መሠረተ ልማትን ለማጠናከር፣ የዲጂታል ክፍያ እና ሰፋፊ የዲጂታል ስትራቴጂዎችን ለማስገንዘብ ሰፊ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት መንግስት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም በርካታ ኢንቨስትመንት መከናወኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዲጂታል ክፍያ ዘርፍ እንዲስፋፋ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በቀጣይ ትኩረት ከሚሰጣቸው ተግባራት መካከል የመረጃ ሉዓላዊነት ጉዳይን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በብዙ መልኩ ኢንቨስት እያደረገች እንደምትገኝም አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስና የክፍያ ሥርዓት በፈጣን የዕድገት ጎዳና ላይ እንደምትገኝም ጠቁመዋል። ከ2026 -2030 የሚተገበረው ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ በሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ይፋ መደረጉን ይታወቃል።  
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትብብር በመስራት ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቷል
Dec 10, 2025 45
ወራቤ፤ ታህሳስ 1/2018 (ኢዜአ):-የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተልዕኮ ተለይተው በትብብርና በቅንጅት በመስራት ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ ትኩረት መሰጠቱን የትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። የኢትዮጵያ ኮምፕሬሄንሲቭ ዩኒቨርሲቲዎች ማህበር 2ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በወራቤ ዩኒቨርሲቲ አካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ተወካይና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) እንደገለፁት፣ ሚኒስቴሩ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በተልዕኮ በመለየት ወደ ተግባር አስገብቷል፡፡ በዚህም ተቋማቱ በምርምር፣ በተግባር፣ በአፕላይድ እና በኮምፕሬሄንሲቭ ደረጃ ተለይተው የመማር ማስተማር ስራቸውን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የአካባቢያቸውን ፀጋ ተጠቅመው ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል ትኩረት መሰጠቱንና የዚህ ጉባኤ ዋና ዓላማም ይህንን ተፈፃሚ ማድረግ መሆኑን አመልክተዋል። ተቋማቱ በየተሰጣቸው ተልዕኮ ተቀናጅተው በትብብር በመስራት ለትምህርት ጥራት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለማድረግ ሚኒስቴሩ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡   የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የኮምፕሬሄንሲቭ ዩኒቨርሲቲዎች ማህበር ሰብሳቢ ድሪባ ኢቲቻ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የመማር ማስተማር ስራውን በላቀ መልኩ ለማከናወን በትብብር መስራት ወሳኝ መሆኑንና ማህበሩም ለእዚህ መቋቋሙን ገልጸዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ያላቸውን አቅም ተጠቅመው በትብብር በመስራት በሀገራዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተጨባጭ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ማህበሩ ይሰራል ብለዋል፡፡ በዚህም በመማር ማስተማር ሥራ፣ በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ሌሎች ዘርፎች ላይ በቅንጅት በመስራት ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት ትኩረት መደረጉን ነው ያስረዱት። የቀብሪደሀር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኢንጂነር አብድልፈታ አህመድ ጠቅላላ ጉባኤው በትብብርና በቅንጅት በመስራት በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለን ውስን ሀብት በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችል ነው ብለዋል።   ዩኒቨርሲቲው በመማር ማስተማር ስራው ብቁ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት የተሰጠውን ተልዕኮ በመወጣት ላይ መሆኑንም አንስተዋል። ኮምፕሬሄንሲቭ ዩኒቨርሲቲዎች በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት የበቁ ዜጎችን ማፍራት ተልዕኮ እንደተሰጣቸው የተናገሩት ደግሞ የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ቶፊቅ ጀማል (ዶ/ር) ናቸው፡፡   ዩኒቨርሲቲው በምርምር የተገኘና ቀደም ሲል በአካባቢው ያልተለመደ የተልባ ዝርያን ጨምሮ የኦቾሎኒ ሰብሎችን በአካባቢው እንዲላመድ በማድረግ ከሀገር ባለፈ ለኤክስፖርት ምርት አስተዋጾ ማድረጉንም አንስተዋል። የማህበሩ መቋቋም አንዱ ከሌላው እንዲማርና ከሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተሞክሮዎችን በማስፋት እንደሀገር በተለያዩ ዘርፎች የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ያስችላል ብለዋል፡፡ በጠቅላላ ጉባኤው በትምህርት ሚኒስቴር ኮምፕሬሄንሲቭ በሚል የተለዩት የ21 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶች መሳተፋቸው ታውቋል፡፡  
በኦሮሚያ ክልል ሴቶች እና ህጻናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመቀነስ ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረዋል
Dec 10, 2025 53
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 1/ 2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ሴቶች እና ህጻናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመቀነስ እና በሁሉም ዘርፎች ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ ስራዎች መጠናከራቸውን የክልሉ ሴቶችና የህፃናት ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። በኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ የሚዘጋጀው 'ጉሚ በልበሎሚ' የተሰኘ የውይይት መርሃ ግብር ላይ የክልሉ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ እና የክልሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ሀላፊዎች ጋር ውይይት ተደርጓል። ቢሮው በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ በክልሉ 16 ዞኖች እና 14 ከተሞች ያካሄደውን የዳሰሳ ጥናት ለውይይቱ መነሻ አቅርቧል። በዳሰሳ ጥናቱ መሰረት፣ በተለይም ከለውጡ ወዲህ በክልሉ ሴቶችና ህፃናት መብቶችን ለመጠበቅ በተሰሩ ስራዎች ላይ ጥሩ መሻሻሎች መታየታቸው የተመለከተ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ችግሩ አሁንም እየተስተዋለ መሆኑ ተጠቅሷል። በተለይም በእነዚህ ወንጀሎች ላይ በቀበሌና በወረዳ ደረጃ በሚገኙ የመንግስት ሴክተር መስሪያ ቤቶች ተሳትፎ ዝቅተኛ መሆኑም ተነስቷል። የደሰሳ ጥናቱን አስመልክተው ማብራሪያ የሰጡት የክልሉ ሴቶችና የህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ፣ በክልሉ የሴቶችና ህፃናት መብቶችን ለመጠበቅ እና የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። በተለይም ከለውጡ ወዲህ መንግስት የሴቶችንና የህፃናትን መብቶች ለመጠበቅና በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመቀነስ ሴቶችን የማብቃት፣ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ወንጀል ፈጻሚዎችን በህግ ተጠያቂ የማድረግ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። ቢሮው የሴቶችንና ህፃናትን መብቶች ለመጠበቅ፣ በሴቶችና በህፃናት ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ለመቀነስ እና ለተጎጂዎች አስፈላጊውን ድጋፍ ለመስጠት ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም አክለዋል። ከዚህ ጎን ለጎን የማህበረሰብ ተሳትፎ አስፈላጊ በመሆኑ ማህበረሰቡን በማሳተፍ ይህንን ችግር ለመግታት ተከታታይ ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል። በኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ቢሮ የምርመራ፣ ክትትል የስራ ሂደት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ዋንዳፍራሽ በበኩላቸው፥ በክልሉ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ ጉድለቶችን ለማረም በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህ ሂደት ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸውም አስረድተዋል።
በክልሉ የሚገኙ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች የተገልጋዩን ጊዜና ወጪ በመቆጠብ ጠቀሜታቸው የጎላ ነው 
Dec 10, 2025 50
ባሕር ዳር፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የሚገኙ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች የመደበኛ ፍትሕ ስርዓቱን ስራ ከማቃለል ባለፈ የተገልጋዩን ጊዜና ወጪ በመቆጠብ ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አለምአንተ አግደው ገለጹ። በአማራ ክልል ባሕላዊ ፍርድ ቤቶችን ስራ የሚያሳልጥ መመሪያ በቅርቡ ተግባራዊ እንደሚደረግም አቶ አለምአንተ አግደው ተናግረዋል። በክልሉ የባሕላዊ ፍርድ ቤቶች ማስተግበሪያ ጥናት፣ ትግበራ ዕቅድ እና ዕወቅና መስጫ መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በባሕርዳር ከተማ ውይይት ተደርጓል።   የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አለምአንተ አግደው እንዳመለከቱት፤ በክልሉ በርካታ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች አሉ። በዚህም የየአካባቢው ሕብረተሰብ እንደየነባራዊ ሁኔታው ግጭቶች ሲፈታባቸው የነበረ ቢሆንም በሕጋዊ ማዕቀፍ እውቅና ኑሯቸው በተደራጀ አግባብ ስራቸውን እንዲያከናውኑ አሰራር ሳይዘረጋ መቆየቱን አስታውሰዋል። አሁን ላይ የወጣውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ለባሕላዊ የግጭት መፍቻ ፍርድ ቤቶች እውቅና የሚሰጥ አሰራር መዘርጋቱንና ለዚሁ የሚሆን የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን ተናግረዋል። ባሕላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች በቅርበት ለማሕበረሰቡ ተደራሽ በመሆን ዳኝነት በመስጠት፣ የመደበኛ ፍትሕ ስርዓቱን ስራ ከማቃለል ባለፈ የተገልጋዩን ጊዜና ወጪ በመቆጠብ ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በተደራጀና ሕጋዊ በሆነ አግባብ ስራቸውን እንዲያከናውኑ እንደሚደረግ ጠቁመው፤ የመመሪያው ዝግጅት በመጠናቀቁ በቅርቡም ወደ ስራ እንደሚገባ አስታውቀዋል። በክልሉ ሽምግልናን ጨምሮ አስራ አምስት ባሕላዊ የግጭት መፍቻ ስርዓቶች እንዳሉ በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው፤ ለእነዚሕ ስርዓቶች ሕጋዊ እውቅና በመስጠት ሕብረተሰቡን እንዲያገለግሉ ይደረጋል ብለዋል።   ባሕላዊ የግጭት መፍቻ ስርዓቶች እውቅና እንዲያገኙና በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆነው ግጭቶችን እንዲፈቱ መደረጉ የክልሉ ባሕላዊ የችግር መፍቻ ስርዓቶች እንዲሰፉ እድል የፈጠረ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አየለ አናውጤ(ዶ/ር) ናቸው። የባሕላዊ የግጭት መፍቻ ስርዓቶች ሕጋዊ እውቅና ተሰጥቷቸው እንዲሰሩ ማስቻል ባሕሉን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍም ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አንስተዋል። ክልል አቀፍ የሽምግልና መማክርት ጉባኤ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን ጠቀሰው፤ ይህም ባሕላዊ የሽምግልና ስርዓቱን በማሳለጥ ድርሻው የጎላ እንደሚሆን አስረድተዋል።
የሚታይ
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በዲጂታል ክፍያ ያስመዘገበችው አስደናቂ ስኬት ተጨማሪ ግቦችን ለማሳካት መሠረት የሚሆኑ ናቸው
Dec 10, 2025 54
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በዲጂታል ክፍያ ያስመዘገበችው አስደናቂ ስኬት ተጨማሪ ግቦችን ለማሳካት መሠረት የሚሆኑ ናቸው ሲሉ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ። ሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል።   በጉባኤው ማጠናቀቂያ ንግግር ያደረጉት የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል ክፍያ ዘርፍ እያስመዘገበች ያለችው ዕድገት አስደናቂ ነው። አሁን ላይ አብዛኛው ዜጋ ከፍተኛ መጠን ያለው ጥሬ ገንዘብ መያዝ አቁሟል ያሉት ገዥው፤ ኢትዮጵያውያን የዲጂታላይዜሽን እና የዳታ ሽግግርን በፍጥነት እየተላመዱ እንደሚገኙም አስረድተዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በተዘረጋው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በየዓመቱ ከ18 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር መከናወኑን ተናግረዋል። ይህን የገንዘብ ዝውውር በጥሬ ገንዘብ ቢከናወን ከፍተኛ ወጪና መጨናነቅ ይፈጥር እንደነበር ጠቁመው፤ ይህ ስኬት ከጥቂት ዓመታት በፊት ፈጽሞ የማይታሰብ እንደነበር ጠቅሰዋል። የመሠረተ ልማትን ለማስፋፋት የተሰጠው ትኩረት ዋነኛ የስኬቱ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥትን ወደ ዲጂታል ግብይት እና የገንዘብ ዝውውር አገልግሎት ለማሸጋገር የሰጠው ትኩረት ለተመዘገበው ውጤት ትልቅ እርምጃ መሆኑን ጠቅሰው፤ በትክክል የታሰበበት፣ በጥንቃቄ የተቀረጸና ተግባራዊ የተደረገ የስትራቴጂ ውጤት ስለመሆኑም ጠቁመዋል። እስካሁን የተገኘውን ውጤት ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰራ ጠቁመው፤ ውጤቱ የሚያዘናጋ ሳይሆን መስፈንጠሪያ ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል። በቀጣይ የዲጂታል ባንኪንግ ተጠቃሚዎችን እምነት ለማሳደግ እና የሥርዓቱን ደኅንነት ይበልጥ ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ጠቅሰው፤ በገጠርና በከተማ ያለውን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልዩነት ለመቀነስ ይሠራል ብለዋል። እንዲሁም የፈጠራ ሥራዎችን በበቂ ሀብት የመደገፍ ሥራዎች ወሳኝ በመሆናቸው በልዩ ትኩረት ይሠራል ብለዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በቁርጠኝነት ሠርታ ያስመዘገበቻቸው ትላልቅ ውጤቶች በቀጣዮቹ ዓመታት ለማሳካት ያስቀመጠቻቸውን ግቦች ለማሳካት ትልቅ መሠረት የሚሆኑ ናቸውም ብለዋል። ኢትዮጵያ የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን ለመገንባት ትክክለኛ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመቅረፅ ትክክለኛውን እርምጃ መውሰዷንም ገልጸዋል። ሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ የመረጃ መሠረተ ልማትን ለማጠናከር፣ የዲጂታል ክፍያ እና ሰፋፊ የዲጂታል ስትራቴጂዎችን ለማስገንዘብ ሰፊ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት መንግስት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም በርካታ ኢንቨስትመንት መከናወኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዲጂታል ክፍያ ዘርፍ እንዲስፋፋ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በቀጣይ ትኩረት ከሚሰጣቸው ተግባራት መካከል የመረጃ ሉዓላዊነት ጉዳይን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በብዙ መልኩ ኢንቨስት እያደረገች እንደምትገኝም አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስና የክፍያ ሥርዓት በፈጣን የዕድገት ጎዳና ላይ እንደምትገኝም ጠቁመዋል። ከ2026 -2030 የሚተገበረው ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ በሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ይፋ መደረጉን ይታወቃል።  
የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ልማት መርሃ ግብር እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኅይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት ያለመ ነው  
Dec 10, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ልማት መርሃ ግብር ከኢኮኖሚው ጋር አብሮ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኅይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት ያለመ መሆኑን የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሽፈራው ተሊላ ገለጹ። የመጀመሪያው ብሔራዊ የኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር ሚና እና ኃላፊነት የተቋም ትግበራ አውደ ጥናት የምክክር መድረክ ሁለተኛ ቀን ቀጥሏል።   የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኅይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሽፈራው ተሊላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የኒውክሊየር ኃይል ተፈጥሮ ለአንድ ሀገር ዘላቂ ልማት እና እድገት ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ የምትከተለው አረንጓዴ ኢኮኖሚ መሆኑን ገልጸው፤ የኢንዱስትሪዎቿ ቁጥር እና ዓይነት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ወደ ኋላ እንዳይመለስ የኃይል ምንጭን አስቀድሞ ማዘጋጀት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ልማት መርሃ ግብር እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ምላሽ መስጠት የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አብዱረዛቅ ኡመር በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ከአካባቢ ጥበቃ ጋር የተስማማ በቂ እና አስተማማኝ ኃይል ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ ወደ ፊት መራመድ እንደምትፈልግ ተናግረዋል።   የኢትዮጵያን ሰላማዊ የኒውክሌር ኃይል አማራጭ የሀገሪቱን የልማት ትልሞች የሚያሳካ መሆኑን ጠቁመዋል። በመካሄድ ላይ ባለው ዓውደ ጥናት የተለያዩ ሀገራት ልምድ እና ተሞክሮዎች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም አንድ ሰላማዊ የኒውክሊየር መሰረተ ልማት ለማቋቋም መከናወን ባለባቸው ተግባራት ላይ ግንዛቤ እየተፈጠረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።  
ኢትዮጵያና ዛምቢያ በወታደራዊ መስክ በትብብር ለመሥራት ተስማሙ
Dec 10, 2025 101
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያና ዛምቢያ በወታደራዊ መስክ በትብብር ለመሥራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ። ስምምነቱ ለረጅም ዓመታት የቆየውን የሀገራቱን ግንኙነት ለማጠናከርና በልዩ ልዩ ወታደራዊ መስኮች ለጋራ ተጠቃሚነት መሥራትን ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በዚህም መሠረት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከዛምቢያ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄፍሪ ዚኤሌ ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ፤ በየተዋረድ ያሉ የየሀገራቱ የመከላከያ አመራሮች የስምምነት ፊርማ ማከናወናቸው ተጠቁሟል።   በዚሁ ወቅትም ለቀጣናው ደኅንነት እንዲሁም ለሀገራት ሠላምና መረጋጋት ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ አስገንዝበዋል። ከዛምቢያ ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማሳደግ እንሠራለን ማለታቸውንም የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ አመላክቷል። የዛምቢያው ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ሌተናል ጄነራል ጄፍሪ ዚኤሌ በበኩላቸው፤ ትብብራችን የተሻለ ዐቅም ለመፍጠርና የጋራ ጥቅማችንን ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል። ከዓድዋ ጦርነት ጀምሮ ያለውን የኢትዮጵያን ሠራዊት ልምድና ተሞክሮ እንዲሁም የኢትዮጵያውያንን የጀግንነት ሥነ-ልቦና አድንቀው፤ ይህም በትብብር እንድንሠራ ያነሳሳን ነው ብለዋል። በልዩ ልዩ ወታደራዊ መስኮች በጋራ ለመሥራት ዛምቢያ ያቀረበችውን ጥያቄ ኢትዮጵያ በመቀበሏ መደሰታቸውንም ጠቁመዋል። የሁለቱን ሀገራት ኤታማዦር ሹሞች ውይይት ተከትሎ የመከላከያ ሚኒስትር ዴዔታ ማርታ ሉዊጂ ከዛምቢያ አቻቸው ማምቦ ሃማውንዱ ጋር በዘመናዊ ሠራዊት ግንባታ፣ በደኅንነት፣ በወታደራዊ ትምህርትና ሥልጠና፣ በወታደራዊ ኢንዱስትሪና በሌሎችም ዘርፎች በጋራ መሥራት የሚያስችል የስምምነት ፊርማ አድርገዋል። ወይዘሮ ማርታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የስምምነቱ ዋነኛ ዓላማ የሁለቱን እህትማማች ሀገራት ብሔራዊ ፍላጎት ለማስጠበቅና የጋራ ተጠቃሚነትን የበለጠ ለማሳደግ ነው። የዛምቢያ መከላከያ ሚኒስትር ዴዔታ ማምቦ ሃማውንዱ በበኩላቸው፤ ለመከላከያ ዘርፋችን ስኬት በሁሉም የትኩረት ዘርፎቻችን ያለንን ግንኙነት አጠናክረን እናስቀጥላለን ብለዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በዓለም ቅርስነት በመመዝገቡ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ
Dec 10, 2025 67
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በዓለም ቅርስነት በመመዝገቡ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ የወላይታ ህዝብ ጥንታዊ ስልጣኔ መገለጫ፣ የበለፀገ ታሪክ እና ከህዝቡ ማንነት ጋር ስር የሰደደ ትስስር ያለው የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ጊፋታ" በዩኔስኮ (UNESCO) በይፋ በመመዝገቡ የተሰማኝን ልባዊ ደስታ ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል።   ጊፋታ ከአሮጌው ወደ አዲሱ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሸጋገርን የሚያበስር፤ እንዲሁም እርቅ እና ፍቅር የሚሰበክበት ታላቅ እሴት መሆኑን ገልጸዋል። "ጊፋታ" በዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ለኢትዮጵያ የቱሪዝም ዕድገት ተጨማሪ አቅም ከመፍጠሩም በላይ ድሉ ለመላው የወላይታ ህዝብ እና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ ትልቅ ኩራት እንደሆነም አመልክተዋል።
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራ በይፋ ተጀመረ
Dec 10, 2025 76
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ):- የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራን ዛሬ በጋራ ማስጀመራቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቁ። ሁለቱ ተቋማት ባወጡት የጋራ መግለጫ ፋይዳ ዲጂታል የማንነት መረጃ ከሁሉም ባንኮች የደንበኞች ባንክ ሂሳብ ቁጥር ጋር የማጣመር (Harmonization) ስራን በይፋ መጀመሩን ገልጸዋል። ይህ የመረጃ ሥርዓቶችን የማጣመር ስራ ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ገንዘብ ማስተላለፍ እንዲችሉ፣ በሀሰተኛ ሰነድ የራሳቸውን ሂሳብ ሌሎች ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ፣ በቀላሉ የብድር አገልግሎትን ማግኘት እንዲችሉ እና በአንድ ፋይዳ መታወቂያ የሁሉንም ባንክ ሂሳብ መጠቀም እንዲያስችላቸው ተመላክቷል። ባንኮች በዚህ መረጃ ጥምረት የደንበኞቻቸውን ትክክለኛ እና ወቅታዊ መረጃን እንዲያገኙ፣ በሀሰተኛ ማንነት የሚከሰት የገንዘብ መጭበርበርን ከመከላከል ባለፈ ለፋይናንስ ሴክተር ዲጂታል ትግበራ ቁልፍ የዲጂታል መሰረተ ልማት ሆኖ እንደሚያገለግል መግለጫው ያትታል። ይህን የባንክ ሂሳብ ቁጥር ከፋይዳ መረጃ ጋር ለማጣመር ደንበኞች ወደ ባንክ ቅርንጫፎቻቸው በአካል በመሔድ ወይም ኦንላይን(ባንኩ በሚያስቀምጠው አሰራር መሰረት) የፋይዳ ተለዋጭ ቁጥር (16 አሀዝ-FAN Number) በማቅረብ ማከናወን ይችላሉ። ደንበኞች በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ማለትም እስከ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የባንክ ሂሳባቸውን ከፋይዳ መረጃ ጋር እንዲያጣምሩ ብሔራዊ ባንክ አሳስቧል። ለፋይዳ ያልተመዘገበ ማንኛውም የባንክ ደንበኛ በቅድሚያ በአቅራቢያው በሚያገኘው የፋይዳ ምዝገባ ጣቢያ በመሄድ መመዝገብ እንዳለበትና ባንኮች በዚህ ሂደት ደንበኞች መጉላላት እንዳያጋጥማቸው አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ በመፈፀም ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል። በሁሉም ባንኮች አዲስ ሂሳብ መክፈት(New Account Opening) (በ “VeriFayda 2” እንዲጀመር፣ እንዲሁም ነባር ሂሳቦችን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር (Existing Account Harmonization) ትግበራም በ “VeriFayda 2” ተግባራዊ የሚደረግበት የጊዜ ሰሌዳ ወጥቶ ለሁሉም ባንኮች ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም መሰራጨቱ በመግለጫው ላይ ሰፍሯል። ቀደም ሲል ሁሉም ባንኮች አዲስ ሂሳብ ለመክፈት የ VeriFayda 1 ስርዓትን ሲጠቀሙ መቆየታቸውም ተመላክቷል፡፡ ከዚህ በኋላ ባንኮች ይበልጥ ዘመናዊና የተቀናጀ ወደ ሆነ ስርዓት “VeriFayda 2” (በኢቲስዊች - EthSwitch በh-A eKYC Service) የማሸጋገር ሥራን በተሳካ ሁኔታ እንዲያከናውኑ የፕሮግራሙና የኢቲስዊች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ለባንክ ተቋማት የቴክኒክ ድጋፍ እና ክትትል እያደረጉ ይገኛል። በቀጣይም የቴክኒክ ድጋፉ እንደሚቀጥል ባንኩ አስታውቋል። በተመሳሳይ ሁሉም ባንኮች ለደንበኞቻቸው አዲስ የባንክ ሂሳብ ለመክፈትም ሆነ ከነባር ሂሳብ ጋር የማጣመር ስራን በመስራት ከVeriFayda 1 (old eKYC) ሙሉ በሙሉ ወደ VeriFayda 2 (new eKYC Service) መሸጋገር እንደሚኖርባቸው ባንኩ አሳስቧል። ይህንን ተከትሎ ቀደም ሲል ባንኮች ሲጠቀሙበት የነበረው የ VeriFayda 1 (eKYC Service) ስርዓት አገልግሎት መስጠት እንደሚያቆምም አመልክቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ይህን የማጣመር ስራ በፍጥነት ወደ ትግበራ ማስገባታቸው ለፋይናንስ ዘርፉ ብቻ ሳይሆን ሀገሪቱ ወደ ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ላይ ትልቁን ሚና እንደሚጫወት ተመላክቷል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
ኢትዮጵያና ዛምቢያ በወታደራዊ መስክ በትብብር ለመሥራት ተስማሙ
Dec 10, 2025 101
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያና ዛምቢያ በወታደራዊ መስክ በትብብር ለመሥራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ። ስምምነቱ ለረጅም ዓመታት የቆየውን የሀገራቱን ግንኙነት ለማጠናከርና በልዩ ልዩ ወታደራዊ መስኮች ለጋራ ተጠቃሚነት መሥራትን ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በዚህም መሠረት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከዛምቢያ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄፍሪ ዚኤሌ ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ፤ በየተዋረድ ያሉ የየሀገራቱ የመከላከያ አመራሮች የስምምነት ፊርማ ማከናወናቸው ተጠቁሟል።   በዚሁ ወቅትም ለቀጣናው ደኅንነት እንዲሁም ለሀገራት ሠላምና መረጋጋት ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ አስገንዝበዋል። ከዛምቢያ ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማሳደግ እንሠራለን ማለታቸውንም የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ አመላክቷል። የዛምቢያው ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ሌተናል ጄነራል ጄፍሪ ዚኤሌ በበኩላቸው፤ ትብብራችን የተሻለ ዐቅም ለመፍጠርና የጋራ ጥቅማችንን ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል። ከዓድዋ ጦርነት ጀምሮ ያለውን የኢትዮጵያን ሠራዊት ልምድና ተሞክሮ እንዲሁም የኢትዮጵያውያንን የጀግንነት ሥነ-ልቦና አድንቀው፤ ይህም በትብብር እንድንሠራ ያነሳሳን ነው ብለዋል። በልዩ ልዩ ወታደራዊ መስኮች በጋራ ለመሥራት ዛምቢያ ያቀረበችውን ጥያቄ ኢትዮጵያ በመቀበሏ መደሰታቸውንም ጠቁመዋል። የሁለቱን ሀገራት ኤታማዦር ሹሞች ውይይት ተከትሎ የመከላከያ ሚኒስትር ዴዔታ ማርታ ሉዊጂ ከዛምቢያ አቻቸው ማምቦ ሃማውንዱ ጋር በዘመናዊ ሠራዊት ግንባታ፣ በደኅንነት፣ በወታደራዊ ትምህርትና ሥልጠና፣ በወታደራዊ ኢንዱስትሪና በሌሎችም ዘርፎች በጋራ መሥራት የሚያስችል የስምምነት ፊርማ አድርገዋል። ወይዘሮ ማርታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የስምምነቱ ዋነኛ ዓላማ የሁለቱን እህትማማች ሀገራት ብሔራዊ ፍላጎት ለማስጠበቅና የጋራ ተጠቃሚነትን የበለጠ ለማሳደግ ነው። የዛምቢያ መከላከያ ሚኒስትር ዴዔታ ማምቦ ሃማውንዱ በበኩላቸው፤ ለመከላከያ ዘርፋችን ስኬት በሁሉም የትኩረት ዘርፎቻችን ያለንን ግንኙነት አጠናክረን እናስቀጥላለን ብለዋል።
የአካባቢያችንን ጸጋ በመለየት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እንሰራለን-አመራሮች
Dec 10, 2025 89
ሚዛን አማን፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- እይታችንን አስፍተን የአካባቢያችንን ጸጋ በመለየት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ የቤንች ሸኮ ዞን አመራሮች ገለጹ። ላለፉት ቀናት "የመደመር መንግስት እይታ በዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የተሰጠውን ስልጠና የተከታተሉ የቤንች ሸኮ ዞን አመራር አባላት ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ እይታችንን አስፍተን የአካባቢያችንን ጸጋ በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። የደቡብ ቤንች ወረዳ አመራር የሆኑት አቶ ኃይሌ ግዛት እንዳሉት፤ የመደመር መንግስት ሀሳብን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማሳካት የሚያስችል በቂ ሥልጠና መሰጠቱ አጋዥ አቅም እንደሆናቸው ጠቁመዋል።   አካባቢያችን የቱሪዝም፣ የማዕድን እና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ያልተነኩ ሀብቶች ያለበት በመሆኑ ሠርቶ ውጤት ማምጣት ከአመራሩ ይጠበቃል ብለዋል። የዜሮ እና የመጨመር ተግባራትን በአግባቡ ለይቶ በመምራት ከግብ እንዲደርሱ ህዝቡን በማስተባበር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በምግብ ራስን የመቻል ውጥንን እውን ለማድረግ ከሰብል ልማት ባሻገር የፍራፍሬ፣ የጓሮ አትክልት፣ የቅመማ ቅመም፣ የማርና ቡናን ጨምሮ ሌሎች በርካታ የአካባቢው እምቅ አቅሞችን በእጥፍ ምርት ለማረጋገጥ መሥራት አለብን ነው ያሉት። ከመደመር መንግስት ግቦች መካከል ተረጂነትን ዜሮ ማድረግ፣ መሬት ጾም እንዳያድር ማድረግና ለሌማት ትሩፋት ሥራ ያለውን ተስማሚነት ተጠቅሞ ምርቶችን ማሳደግ እንደሚጠበቅ የሼይ ቤንች ወረዳ አመራር አቶ ወንድሙ ጌታ ተናግረዋል።   እነዚህን የመንግስት የልማት ግቦች ወደ ውጤት ቀይሮ የሕዝብ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ራዕይ ይዘው ወደ ተግባር ለመግባት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። እይታችንን ባለ ማስፋታችን ለውጥ ያላመጣንባቸውን የልማት ዘርፎች በመደመር መንግሥት እይታ ለይተን ተጠቃሚ ለመሆን ተዘጋጅተናል ያሉት ደግሞ ሌላዋ አመራር ወይዘሮ ባንቻየሁ ሉቃስ ናቸው። የተለያዩ የልማት ተሞክሮዎችን በመቀመር በቀበሌ ደረጃ ለማስፋት እንደሚተጉም ተናግረዋል።
ስምምነቱ ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ ያስችላል 
Dec 10, 2025 92
ደሴ ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዘላቂ ሰላም በማስፈን የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ልማቶችን ለማካሄድ የሚያስችል መሆኑን የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ከደሴ ከተማ ነዋሪዎች መካከል መቶ አለቃ ጌቱ አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ለዘመናት የገነባናቸው የአብሮነት፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የመከባበር የጋራ እሴቶቻችንን በማስቀጠል ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ማድረግ ከሁላችንም ይጠበቃል ብለዋል።   መንግስት ሰላምን ለማጽናትና ልማትን ለማስቀጠል የሰጠው ትኩረት የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት መካከል የተደረሰው ስምምነትም ዘላቂ ሰላም ለማስፈንና ልማትን ለማስቀጠል የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፤ ስምምነቱ ለህዝቡ እፎይታን በመስጠት ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጡ ልማቶችን ለማካሄድ ያስችላል ብለዋል። የከተማው ነዋሪ አቶ ኢብራሂም አሊ በበኩላቸው፣ የከተማዋን ሰላም በጋራ በማጽናት የተጀመሩ ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁለንተናዊ ተሳትፏችንን እንቀጥላለን ብለዋል።   ስምምነቱ ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ ከማስቻሉ ባለፈ ለሌሎችም ትምህርት የሚሆን ነው ብለዋል። የችግሮች መፍቻ የሆኑ እሴቶችና ባህሎችን በማጎልበት ለንግግርና ለውይይት ቅድሚያ በመስጠት ሰላም እንዲሰፍን ኃላፊነታችን እንወጣለን ያሉት ደግሞ መምህር አሸናፊ ጸጋዬ ናቸው።   የውጭና የውስጥ ጠላቶቻችን በተቀነባበረ መንገድ ግጭት እንዲባባስ የሚያደርጉትን ጥረት በጋራ ማክሸፍ ይገባናል ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ሰሚራ ሰይድ ናቸው። ሰሞኑን በተፈጠረው የሰላም ስምምነት እጅግ መደሰታቸውን ጠቁመው፤ ስምምነቱ ለሌሎችም ትምህርት የሰጠና መለመድ ያለበት መሆኑን ገልጸዋል።   ታላቅ የሰላም ጥሪን ያነገበ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰላማዊ ሰልፍ በደሴ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል።
ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ይበጃሉ ያላቸውን አጀንዳዎች የልየታ ስራ እያጠናቀቀ ነው
Dec 9, 2025 166
አዲስ አበባ፤ ህዳር 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ይበጃሉ ያላቸው አጀንዳዎች የልየታ ስራ እየተጠናቀቀ መሆኑን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በእስካሁን ሂደት የተከናወኑ ተግባራትንና የተገኙ ውጤቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ገለጻ እያደረገ ነው።   በመርሃ ግብሩ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች፣ አምባሳደሮች፣ ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ተሳታፊዎች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በዚሁ ወቅት፤ ሀገራዊ ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና ዴሞክራሲን ለማስፈን በምክክር ላይ የተመሰረተ መፍትሔ ለማምጣት እየተሰራ ነው ብለዋል።   ለዚህም ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የሁሉም ድምጽ የሚሰማበት አካታችና አሳታፊ ሂደትን እየተከተለ እንደሚገኝ ገልጸው፤ ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ተዓማኒነት ያላቸው አሰራሮችን በመከተል ሥራውን እያከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በሂደቱም አሳታፊ በሆነ መንገድ በኢትዮጵያ በቆዩ ችግሮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ይበጃሉ የተባሉ አጀንዳዎች ልየታ ስራን እያጠናቀቀ መሆኑንም አስረድተዋል።   የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ስራው ውጤታማ እንዲሆን መስራት ሌላው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑንም አብራርተዋል።
ቀኑ በህዝቦች መካከል አብሮነትን እና አንድነትን ለማጠናከር የተጀመረውን ጥረት በሚያጎለብት መልኩ ተከብሯል 
Dec 9, 2025 120
ሆሳዕና ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በህዝቦች መካከል አብሮነትን እና አንድነትን ለማጠናከር የተጀመረውን ጥረት በሚያጎለብት መልኩ መከበሩን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ የበዓሉን በስኬት መጠናቀቅ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ በዓሉ በትብብር መስራት ተጨባጭ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ተሞክሮ የተወሰደበት ነው ብለዋል፡፡ በዓሉ በስኬት እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ህብረተሰቡን በማስተባበር ከተሞችን ውብና ፅዱ ከማድረግ ጀምሮ በዓሉን ለማድመቅ የሚሆኑ የመሰረተ ልማቶችን በአጭር ጊዜ ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል። የክልሉ ህዝብም እንግዶችን ተቀብሎ በማስተናገድ ያሳየው ተሳትፎ የጋራ ትርክት ለመገንባት የተጀመረውን ጥረት ለማጠናከር ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። ከሁሉም በላይ በዓሉ በህዝቦች መካከል አብሮነትን እና አንድነትን ለማጠናከር የተጀመረውን ጥረት በሚያጎለብት መልኩ መከበሩንም አክለዋል። የመንግሥትን አቅምና የማህበረሰቡን ተሳትፎ በማቀናጀት መስራት ከተቻለ ለስኬት መብቃት እንደሚቻል በተጨባጭ የታየበት መሆኑን አስረድተዋል። በዓሉ በስኬታማነት እንዲጠናቀቅ በተለያየ መንገድ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና ያቀረቡት ርዕሰ መስተዳደሩ በተለይም የፌዴሬሽን ምክር ቤትን ጨምሮ የአጎራባች ክልሎችና የጸጥታ መዋቅር አካላት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና ይገባል ብለዋል፡፡ የሚዲያ አካላትም ክልሉን በማስተዋወቅ፣ የክልሉ ህዝብ እንግዶችን በመቀበል እንዲሁም የክልሉ አመራር በማስተባበር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም በክልሉ በሁሉም መዋቅሮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
ያገኘነውን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ አካባቢያችንን ለማልማት ቁርጠኞች ነን
Dec 9, 2025 130
ዲላ/ ወላይታ ሶዶ ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦ በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ አካባቢያቸውን ለማልማት ቁርጠኞች መሆናቸውን የጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ ሰልጣኝ አመራሮች ገለጹ። በጌዴኦ ዞንና በዲላ ከተማ አስተዳደር "በመደመር መንግስት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ ለ3ኛ ዙር ለመካከለኛ አመራሮች የተሰጠው ስልጠና ተጠናቋል። አመራሮቹ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በስልጠና ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ ለአካባቢያቸው እድገት የበኩላቸውን ይወጣሉ፡፡ ስልጠናው በብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት ያላቸውን ግንዛቤ ከማሳደግ ባለፈ ዞኑ በግብርናና በቱሪዝም ልማት ያለውን አቅም አውጥቶ ለመጠቀም በርብርብ ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።   አስተያየታቸውን ከሰጡ ሰልጣኝ አመራሮች መካከል ወይዘሮ ውዴ አብርሃም፣ ስልጠናው በተለይም በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በከተማ መሠረተ ልማትና በቱሪዝም ዘርፍ ያላቸውን ግንዛቤ ያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል። በተግባር በተደገፈ ስልጠና ያገኙትን እውቀት ወደ መሬት በማውረድ ለአካባቢያቸው ልማትና ለብልፅግና ጉዞ መፋጠን የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ስልጠናው ያሉ ሀብቶችን በማስተባበር እንዴት ወደ ውጤት መቀየር እንደሚቻል አቅም ያገኘንበት ነው ያሉት ደግሞ አቶ ተክሉ አራርሶ ናቸው።   በመፍጠን እና መፍጠር እሳቤ ለዞኑ እድገት እንደሚሰሩ ገልጸው፣ በስልጠናው መነሻ ፀጋዎችን ለይተው በመስራት ለአካባቢያቸው እድገት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ሌላኛዋ ሰልጣኝ ወይዘሮ ራሄል ግርማ በበኩላቸው፤ ስልጠናው የብልፅግና ፓርቲ መዳረሻን በበቂ ሁኔታ የዳሰሰና ግንዛቤን ያስጨበጠ ነው ብለዋል።   ይህም የፓርቲውን እሳቤዎች ተገንዝበን ወደታች በማውረድ ለተጀመረው የብልፅግና ጉዞ መፋጠን በትኩረት ለመስራት አቅም ይሆነናል ብለዋል። የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር)፤ አመራሩ የወሰደውን ስልጠና ወደ ተግባር በመለወጥ በየዘርፉ እመርታዊ ውጤትን ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት መስራት አለበት ብለዋል።   ‎‎‎በተለይም በዞኑ በቡናና እንሰት ልማት፣ በገቢ አሰባሰብ እንዲሁም የቁጠባ ባህልን በማዳበር ረገድ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል። ‎ ‎የዞኑን እምቅ ሀብቶችና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስተዋወቅ የቱሪዝም ዘርፍ እመርታን ማረጋገጥ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ በወላይታ ሶዶ በተሰጠው ስልጠና ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሰማ (ረዳት ፕሮፌሰር) በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት፣ በኢንዱስትሪ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ተለይቶ የተሰጠው ስልጠና የአመራሩን አቅምና ተነሳሽነት ያሳደገ ነው ብለዋል።   በዞኑ በርካታ የመልማትና የማደግ አቅም እንዳለ ጠቅሰው፣ የሜካናይዜሽን እርሻና የግብርና ቴክኖሎጂን በመተግበር የምርት መጠንን ለማሳደግና ህዝቡን ከተረጂነት ለማላቀቅ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል። በሌማት ትሩፋት ዘርፍም የወተት፣ የማር፣ የሥጋ፣ የአሣ፣ የእንቁላል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ መንደር በመፍጠር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ብለዋል፡፡   ከወላይታ ሶዶ ሰልጣኝ አመራሮች መካከል አቶ ሀብታሙ ሙላቱ እንደገለጹት፤ ስልጠናው የውስጥ ፀጋዎችንና አቅሞችን ለይቶ ወደ ውጤት በመቀየር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተነሳሽነትን የፈጠረ ነው።   ወይዘሮ ሰላማዊት መኮንን በበኩላቸው ፤ስልጠናው በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በከተማ ልማት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ያለንን አቅም ተረድተን የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅም ያገኘንበት ነው ብለዋል።   በዞኑ ያሉትን የተፈጥሮ ጸጋዎች ወደ ልማት መቀየር ከተቻለ ህዝቡን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚቻል ገልጸው፣ በስልጠና ያገኙትን አቅም በመተግበር የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
በሕብረተሰቡና በጸጥታ መዋቅሩ የተቀናጀ ርብርብ በጎንደር አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ተችሏል
Dec 9, 2025 121
ጎንደር፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ በሕብረተሰቡና በጸጥታ መዋቅሩ የተቀናጀ ርብርብ እና ድጋፍ አስተማማኝ ሰላም ማስፈን መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በከተማ አስተማማኝ ሰላም መስፈኑን ተከትሎ በምሽት የሰውና የተሸከርካሪ እንቅስቃሴ ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ ሙሉ በሙሉ መነሳቱን መምሪያው ገልጿል። የከተማ አስተዳደሩ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ አለልኝ አለም በሰጡት መግለጫ ፤ በሕብረተሰቡና በጸጥታ መዋቅሩ የተቀናጀ ርብርብና ድጋፍ አሁን ላይ የከተማው ሰላም አስተማማኝ ደረጃ ላይ መድረሱን አስታውቀዋል፡፡ በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችና ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ምሸት ጭምር እየተሰሩ ያሉት ሰላማዊ ድባብ በመፈጠሩ እንደሆነ አንስተዋል። ሰላሙን በዘላቂነት ከማረጋገጥ ጎን ለጎን በከተማው የሰውና የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ባልተገደበ መንገድ 24 ሰዓት እንዲከናወን ለማስቻልም የምሽት የሰዓት ገደብ እንዲነሳ በከተማ አስተዳደሩ መወሰኑን ይፋ አድርገዋል፡፡ በቀጣይ ጥር ወር በሚከበረው የጥምቀት በዓል እንግዶችና ቱሪስቶች ባልተገደበ እንቅስቃሴ በበዓሉ ላይ መታደም እንዲችሉ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም አረጋግጠዋል፡፡ ሕብረተሰቡ በብሎክ ተደራጅቶ እያደረገ ያለውን የሰላም ማስከበር ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበው፤ የጸጥታ መዋቅሩም ተልዕኮውን በሙሉ ሃላፊነት እንደሚወጣም አስታውቀዋል፡፡
ፖለቲካ
ኢትዮጵያና ዛምቢያ በወታደራዊ መስክ በትብብር ለመሥራት ተስማሙ
Dec 10, 2025 101
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያና ዛምቢያ በወታደራዊ መስክ በትብብር ለመሥራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ። ስምምነቱ ለረጅም ዓመታት የቆየውን የሀገራቱን ግንኙነት ለማጠናከርና በልዩ ልዩ ወታደራዊ መስኮች ለጋራ ተጠቃሚነት መሥራትን ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በዚህም መሠረት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከዛምቢያ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄፍሪ ዚኤሌ ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ፤ በየተዋረድ ያሉ የየሀገራቱ የመከላከያ አመራሮች የስምምነት ፊርማ ማከናወናቸው ተጠቁሟል።   በዚሁ ወቅትም ለቀጣናው ደኅንነት እንዲሁም ለሀገራት ሠላምና መረጋጋት ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ አስገንዝበዋል። ከዛምቢያ ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማሳደግ እንሠራለን ማለታቸውንም የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለኢዜአ የላከው መረጃ አመላክቷል። የዛምቢያው ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ሌተናል ጄነራል ጄፍሪ ዚኤሌ በበኩላቸው፤ ትብብራችን የተሻለ ዐቅም ለመፍጠርና የጋራ ጥቅማችንን ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል። ከዓድዋ ጦርነት ጀምሮ ያለውን የኢትዮጵያን ሠራዊት ልምድና ተሞክሮ እንዲሁም የኢትዮጵያውያንን የጀግንነት ሥነ-ልቦና አድንቀው፤ ይህም በትብብር እንድንሠራ ያነሳሳን ነው ብለዋል። በልዩ ልዩ ወታደራዊ መስኮች በጋራ ለመሥራት ዛምቢያ ያቀረበችውን ጥያቄ ኢትዮጵያ በመቀበሏ መደሰታቸውንም ጠቁመዋል። የሁለቱን ሀገራት ኤታማዦር ሹሞች ውይይት ተከትሎ የመከላከያ ሚኒስትር ዴዔታ ማርታ ሉዊጂ ከዛምቢያ አቻቸው ማምቦ ሃማውንዱ ጋር በዘመናዊ ሠራዊት ግንባታ፣ በደኅንነት፣ በወታደራዊ ትምህርትና ሥልጠና፣ በወታደራዊ ኢንዱስትሪና በሌሎችም ዘርፎች በጋራ መሥራት የሚያስችል የስምምነት ፊርማ አድርገዋል። ወይዘሮ ማርታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የስምምነቱ ዋነኛ ዓላማ የሁለቱን እህትማማች ሀገራት ብሔራዊ ፍላጎት ለማስጠበቅና የጋራ ተጠቃሚነትን የበለጠ ለማሳደግ ነው። የዛምቢያ መከላከያ ሚኒስትር ዴዔታ ማምቦ ሃማውንዱ በበኩላቸው፤ ለመከላከያ ዘርፋችን ስኬት በሁሉም የትኩረት ዘርፎቻችን ያለንን ግንኙነት አጠናክረን እናስቀጥላለን ብለዋል።
የአካባቢያችንን ጸጋ በመለየት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እንሰራለን-አመራሮች
Dec 10, 2025 89
ሚዛን አማን፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- እይታችንን አስፍተን የአካባቢያችንን ጸጋ በመለየት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ የቤንች ሸኮ ዞን አመራሮች ገለጹ። ላለፉት ቀናት "የመደመር መንግስት እይታ በዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የተሰጠውን ስልጠና የተከታተሉ የቤንች ሸኮ ዞን አመራር አባላት ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ እይታችንን አስፍተን የአካባቢያችንን ጸጋ በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል። የደቡብ ቤንች ወረዳ አመራር የሆኑት አቶ ኃይሌ ግዛት እንዳሉት፤ የመደመር መንግስት ሀሳብን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማሳካት የሚያስችል በቂ ሥልጠና መሰጠቱ አጋዥ አቅም እንደሆናቸው ጠቁመዋል።   አካባቢያችን የቱሪዝም፣ የማዕድን እና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ያልተነኩ ሀብቶች ያለበት በመሆኑ ሠርቶ ውጤት ማምጣት ከአመራሩ ይጠበቃል ብለዋል። የዜሮ እና የመጨመር ተግባራትን በአግባቡ ለይቶ በመምራት ከግብ እንዲደርሱ ህዝቡን በማስተባበር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በምግብ ራስን የመቻል ውጥንን እውን ለማድረግ ከሰብል ልማት ባሻገር የፍራፍሬ፣ የጓሮ አትክልት፣ የቅመማ ቅመም፣ የማርና ቡናን ጨምሮ ሌሎች በርካታ የአካባቢው እምቅ አቅሞችን በእጥፍ ምርት ለማረጋገጥ መሥራት አለብን ነው ያሉት። ከመደመር መንግስት ግቦች መካከል ተረጂነትን ዜሮ ማድረግ፣ መሬት ጾም እንዳያድር ማድረግና ለሌማት ትሩፋት ሥራ ያለውን ተስማሚነት ተጠቅሞ ምርቶችን ማሳደግ እንደሚጠበቅ የሼይ ቤንች ወረዳ አመራር አቶ ወንድሙ ጌታ ተናግረዋል።   እነዚህን የመንግስት የልማት ግቦች ወደ ውጤት ቀይሮ የሕዝብ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ራዕይ ይዘው ወደ ተግባር ለመግባት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። እይታችንን ባለ ማስፋታችን ለውጥ ያላመጣንባቸውን የልማት ዘርፎች በመደመር መንግሥት እይታ ለይተን ተጠቃሚ ለመሆን ተዘጋጅተናል ያሉት ደግሞ ሌላዋ አመራር ወይዘሮ ባንቻየሁ ሉቃስ ናቸው። የተለያዩ የልማት ተሞክሮዎችን በመቀመር በቀበሌ ደረጃ ለማስፋት እንደሚተጉም ተናግረዋል።
ስምምነቱ ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ ያስችላል 
Dec 10, 2025 92
ደሴ ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዘላቂ ሰላም በማስፈን የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ልማቶችን ለማካሄድ የሚያስችል መሆኑን የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ከደሴ ከተማ ነዋሪዎች መካከል መቶ አለቃ ጌቱ አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ለዘመናት የገነባናቸው የአብሮነት፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የመከባበር የጋራ እሴቶቻችንን በማስቀጠል ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ማድረግ ከሁላችንም ይጠበቃል ብለዋል።   መንግስት ሰላምን ለማጽናትና ልማትን ለማስቀጠል የሰጠው ትኩረት የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት መካከል የተደረሰው ስምምነትም ዘላቂ ሰላም ለማስፈንና ልማትን ለማስቀጠል የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው፤ ስምምነቱ ለህዝቡ እፎይታን በመስጠት ተጠቃሚነቱን የሚያረጋግጡ ልማቶችን ለማካሄድ ያስችላል ብለዋል። የከተማው ነዋሪ አቶ ኢብራሂም አሊ በበኩላቸው፣ የከተማዋን ሰላም በጋራ በማጽናት የተጀመሩ ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁለንተናዊ ተሳትፏችንን እንቀጥላለን ብለዋል።   ስምምነቱ ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ ከማስቻሉ ባለፈ ለሌሎችም ትምህርት የሚሆን ነው ብለዋል። የችግሮች መፍቻ የሆኑ እሴቶችና ባህሎችን በማጎልበት ለንግግርና ለውይይት ቅድሚያ በመስጠት ሰላም እንዲሰፍን ኃላፊነታችን እንወጣለን ያሉት ደግሞ መምህር አሸናፊ ጸጋዬ ናቸው።   የውጭና የውስጥ ጠላቶቻችን በተቀነባበረ መንገድ ግጭት እንዲባባስ የሚያደርጉትን ጥረት በጋራ ማክሸፍ ይገባናል ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ሰሚራ ሰይድ ናቸው። ሰሞኑን በተፈጠረው የሰላም ስምምነት እጅግ መደሰታቸውን ጠቁመው፤ ስምምነቱ ለሌሎችም ትምህርት የሰጠና መለመድ ያለበት መሆኑን ገልጸዋል።   ታላቅ የሰላም ጥሪን ያነገበ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰላማዊ ሰልፍ በደሴ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል።
ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ይበጃሉ ያላቸውን አጀንዳዎች የልየታ ስራ እያጠናቀቀ ነው
Dec 9, 2025 166
አዲስ አበባ፤ ህዳር 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ይበጃሉ ያላቸው አጀንዳዎች የልየታ ስራ እየተጠናቀቀ መሆኑን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በእስካሁን ሂደት የተከናወኑ ተግባራትንና የተገኙ ውጤቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ገለጻ እያደረገ ነው።   በመርሃ ግብሩ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች፣ አምባሳደሮች፣ ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ተሳታፊዎች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በዚሁ ወቅት፤ ሀገራዊ ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና ዴሞክራሲን ለማስፈን በምክክር ላይ የተመሰረተ መፍትሔ ለማምጣት እየተሰራ ነው ብለዋል።   ለዚህም ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የሁሉም ድምጽ የሚሰማበት አካታችና አሳታፊ ሂደትን እየተከተለ እንደሚገኝ ገልጸው፤ ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ተዓማኒነት ያላቸው አሰራሮችን በመከተል ሥራውን እያከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በሂደቱም አሳታፊ በሆነ መንገድ በኢትዮጵያ በቆዩ ችግሮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ይበጃሉ የተባሉ አጀንዳዎች ልየታ ስራን እያጠናቀቀ መሆኑንም አስረድተዋል።   የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ስራው ውጤታማ እንዲሆን መስራት ሌላው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑንም አብራርተዋል።
ቀኑ በህዝቦች መካከል አብሮነትን እና አንድነትን ለማጠናከር የተጀመረውን ጥረት በሚያጎለብት መልኩ ተከብሯል 
Dec 9, 2025 120
ሆሳዕና ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በህዝቦች መካከል አብሮነትን እና አንድነትን ለማጠናከር የተጀመረውን ጥረት በሚያጎለብት መልኩ መከበሩን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ የበዓሉን በስኬት መጠናቀቅ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ በዓሉ በትብብር መስራት ተጨባጭ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ተሞክሮ የተወሰደበት ነው ብለዋል፡፡ በዓሉ በስኬት እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ህብረተሰቡን በማስተባበር ከተሞችን ውብና ፅዱ ከማድረግ ጀምሮ በዓሉን ለማድመቅ የሚሆኑ የመሰረተ ልማቶችን በአጭር ጊዜ ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል። የክልሉ ህዝብም እንግዶችን ተቀብሎ በማስተናገድ ያሳየው ተሳትፎ የጋራ ትርክት ለመገንባት የተጀመረውን ጥረት ለማጠናከር ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። ከሁሉም በላይ በዓሉ በህዝቦች መካከል አብሮነትን እና አንድነትን ለማጠናከር የተጀመረውን ጥረት በሚያጎለብት መልኩ መከበሩንም አክለዋል። የመንግሥትን አቅምና የማህበረሰቡን ተሳትፎ በማቀናጀት መስራት ከተቻለ ለስኬት መብቃት እንደሚቻል በተጨባጭ የታየበት መሆኑን አስረድተዋል። በዓሉ በስኬታማነት እንዲጠናቀቅ በተለያየ መንገድ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና ያቀረቡት ርዕሰ መስተዳደሩ በተለይም የፌዴሬሽን ምክር ቤትን ጨምሮ የአጎራባች ክልሎችና የጸጥታ መዋቅር አካላት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና ይገባል ብለዋል፡፡ የሚዲያ አካላትም ክልሉን በማስተዋወቅ፣ የክልሉ ህዝብ እንግዶችን በመቀበል እንዲሁም የክልሉ አመራር በማስተባበር ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም በክልሉ በሁሉም መዋቅሮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
ያገኘነውን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ አካባቢያችንን ለማልማት ቁርጠኞች ነን
Dec 9, 2025 130
ዲላ/ ወላይታ ሶዶ ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦ በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ አካባቢያቸውን ለማልማት ቁርጠኞች መሆናቸውን የጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ ሰልጣኝ አመራሮች ገለጹ። በጌዴኦ ዞንና በዲላ ከተማ አስተዳደር "በመደመር መንግስት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ ለ3ኛ ዙር ለመካከለኛ አመራሮች የተሰጠው ስልጠና ተጠናቋል። አመራሮቹ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በስልጠና ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ ለአካባቢያቸው እድገት የበኩላቸውን ይወጣሉ፡፡ ስልጠናው በብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት ያላቸውን ግንዛቤ ከማሳደግ ባለፈ ዞኑ በግብርናና በቱሪዝም ልማት ያለውን አቅም አውጥቶ ለመጠቀም በርብርብ ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።   አስተያየታቸውን ከሰጡ ሰልጣኝ አመራሮች መካከል ወይዘሮ ውዴ አብርሃም፣ ስልጠናው በተለይም በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በከተማ መሠረተ ልማትና በቱሪዝም ዘርፍ ያላቸውን ግንዛቤ ያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል። በተግባር በተደገፈ ስልጠና ያገኙትን እውቀት ወደ መሬት በማውረድ ለአካባቢያቸው ልማትና ለብልፅግና ጉዞ መፋጠን የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። ስልጠናው ያሉ ሀብቶችን በማስተባበር እንዴት ወደ ውጤት መቀየር እንደሚቻል አቅም ያገኘንበት ነው ያሉት ደግሞ አቶ ተክሉ አራርሶ ናቸው።   በመፍጠን እና መፍጠር እሳቤ ለዞኑ እድገት እንደሚሰሩ ገልጸው፣ በስልጠናው መነሻ ፀጋዎችን ለይተው በመስራት ለአካባቢያቸው እድገት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ሌላኛዋ ሰልጣኝ ወይዘሮ ራሄል ግርማ በበኩላቸው፤ ስልጠናው የብልፅግና ፓርቲ መዳረሻን በበቂ ሁኔታ የዳሰሰና ግንዛቤን ያስጨበጠ ነው ብለዋል።   ይህም የፓርቲውን እሳቤዎች ተገንዝበን ወደታች በማውረድ ለተጀመረው የብልፅግና ጉዞ መፋጠን በትኩረት ለመስራት አቅም ይሆነናል ብለዋል። የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር)፤ አመራሩ የወሰደውን ስልጠና ወደ ተግባር በመለወጥ በየዘርፉ እመርታዊ ውጤትን ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት መስራት አለበት ብለዋል።   ‎‎‎በተለይም በዞኑ በቡናና እንሰት ልማት፣ በገቢ አሰባሰብ እንዲሁም የቁጠባ ባህልን በማዳበር ረገድ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል። ‎ ‎የዞኑን እምቅ ሀብቶችና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስተዋወቅ የቱሪዝም ዘርፍ እመርታን ማረጋገጥ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። በተመሳሳይ በወላይታ ሶዶ በተሰጠው ስልጠና ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሰማ (ረዳት ፕሮፌሰር) በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በከተማ ልማት፣ በኢንዱስትሪ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ተለይቶ የተሰጠው ስልጠና የአመራሩን አቅምና ተነሳሽነት ያሳደገ ነው ብለዋል።   በዞኑ በርካታ የመልማትና የማደግ አቅም እንዳለ ጠቅሰው፣ የሜካናይዜሽን እርሻና የግብርና ቴክኖሎጂን በመተግበር የምርት መጠንን ለማሳደግና ህዝቡን ከተረጂነት ለማላቀቅ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል። በሌማት ትሩፋት ዘርፍም የወተት፣ የማር፣ የሥጋ፣ የአሣ፣ የእንቁላል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ መንደር በመፍጠር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ብለዋል፡፡   ከወላይታ ሶዶ ሰልጣኝ አመራሮች መካከል አቶ ሀብታሙ ሙላቱ እንደገለጹት፤ ስልጠናው የውስጥ ፀጋዎችንና አቅሞችን ለይቶ ወደ ውጤት በመቀየር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተነሳሽነትን የፈጠረ ነው።   ወይዘሮ ሰላማዊት መኮንን በበኩላቸው ፤ስልጠናው በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በከተማ ልማት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ያለንን አቅም ተረድተን የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅም ያገኘንበት ነው ብለዋል።   በዞኑ ያሉትን የተፈጥሮ ጸጋዎች ወደ ልማት መቀየር ከተቻለ ህዝቡን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚቻል ገልጸው፣ በስልጠና ያገኙትን አቅም በመተግበር የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
በሕብረተሰቡና በጸጥታ መዋቅሩ የተቀናጀ ርብርብ በጎንደር አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ተችሏል
Dec 9, 2025 121
ጎንደር፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ በሕብረተሰቡና በጸጥታ መዋቅሩ የተቀናጀ ርብርብ እና ድጋፍ አስተማማኝ ሰላም ማስፈን መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በከተማ አስተማማኝ ሰላም መስፈኑን ተከትሎ በምሽት የሰውና የተሸከርካሪ እንቅስቃሴ ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ ሙሉ በሙሉ መነሳቱን መምሪያው ገልጿል። የከተማ አስተዳደሩ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ አለልኝ አለም በሰጡት መግለጫ ፤ በሕብረተሰቡና በጸጥታ መዋቅሩ የተቀናጀ ርብርብና ድጋፍ አሁን ላይ የከተማው ሰላም አስተማማኝ ደረጃ ላይ መድረሱን አስታውቀዋል፡፡ በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችና ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ምሸት ጭምር እየተሰሩ ያሉት ሰላማዊ ድባብ በመፈጠሩ እንደሆነ አንስተዋል። ሰላሙን በዘላቂነት ከማረጋገጥ ጎን ለጎን በከተማው የሰውና የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ባልተገደበ መንገድ 24 ሰዓት እንዲከናወን ለማስቻልም የምሽት የሰዓት ገደብ እንዲነሳ በከተማ አስተዳደሩ መወሰኑን ይፋ አድርገዋል፡፡ በቀጣይ ጥር ወር በሚከበረው የጥምቀት በዓል እንግዶችና ቱሪስቶች ባልተገደበ እንቅስቃሴ በበዓሉ ላይ መታደም እንዲችሉ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም አረጋግጠዋል፡፡ ሕብረተሰቡ በብሎክ ተደራጅቶ እያደረገ ያለውን የሰላም ማስከበር ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበው፤ የጸጥታ መዋቅሩም ተልዕኮውን በሙሉ ሃላፊነት እንደሚወጣም አስታውቀዋል፡፡
ማህበራዊ
የፌዴራል መንግስት በክልሉ እያከናወናቸው የሚገኙ ፕሮጀክቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ ነው- ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ
Dec 10, 2025 53
መቀሌ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል እያከናወናቸው የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ ገለጸ። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ፤ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ የልማት ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ሚኒስቴሩ በመቀሌ ከተማ ዳርቻ ላይ በ2 ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ወጪ ለሚገነባ የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በትግራይ ክልል ከውሃና ሳኒቴሽን ጋር የተያያዙ የልማት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑም ተመላክቷል።   በዚህ ወቅት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ ፤ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል እያከናወናቸው የሚገኙት የልማት ፕሮጀክቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን አረጋግጠዋል። መሰል የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል። በመቀሌ ተገኝተው ለፕሮጀክቱ የመሰረተ ደንጋይ ያስቀመጡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ፤ የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል ለማህበራዊ አገልግሎት የሚውሉ የግንባታ ፕሮጀክቶችን ማከናወኑን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ በዛሬው ዕለት በመቀሌ ከተማ ዳርቻ ላይ የሚገነባ የፍሳሽ ማስወገጃና ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምሯል ብለዋል።   ይኸው የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክትም በመቀሌ ከተማ ዳርቻ ላይ በ2 ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ወጪ የሚገነባ መሆኑንም አስታውቀዋል። የከተማው የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክትም በአካባቢው ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች በመስኖ ልማት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅም ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። በክልሉ በአምስት ከተሞች የውሃና ሳኒቴሽን አገልግሎት የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን ሚኒስቴሩ እያከናወነ መሆኑንም አንስተዋል። ሚኒስቴሩና ተጠሪ ተቋማቱ ከዚህ ቀደምም በከተማዋ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ቤቶችን በመገንባት ማስረከባቸው ይታወሳል። በእንደርታ ወረዳ የማይ ዓለም ገጠር ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ቄስ ገብረኪዳን ታደሰ ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ወጣቶች የስራ ዕድል ከመፍጠሩም ባሻገር በመስኖ ልማቱ በመጠቀም ከተረጂነት ለመውጣት የሚደረገውን ጥረት እናግዛለን ብለዋል። ወይዘሮ ለተመሰቀል ሀዱሽ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ ለልጆቻችን ተጨማሪ የሥራ ዕድልን ይፈጥራል ብለን እንጠብቃለን ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትብብር በመስራት ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቷል
Dec 10, 2025 45
ወራቤ፤ ታህሳስ 1/2018 (ኢዜአ):-የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተልዕኮ ተለይተው በትብብርና በቅንጅት በመስራት ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ ትኩረት መሰጠቱን የትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። የኢትዮጵያ ኮምፕሬሄንሲቭ ዩኒቨርሲቲዎች ማህበር 2ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በወራቤ ዩኒቨርሲቲ አካሂዷል።   በመድረኩ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ተወካይና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) እንደገለፁት፣ ሚኒስቴሩ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በተልዕኮ በመለየት ወደ ተግባር አስገብቷል፡፡ በዚህም ተቋማቱ በምርምር፣ በተግባር፣ በአፕላይድ እና በኮምፕሬሄንሲቭ ደረጃ ተለይተው የመማር ማስተማር ስራቸውን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የአካባቢያቸውን ፀጋ ተጠቅመው ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል ትኩረት መሰጠቱንና የዚህ ጉባኤ ዋና ዓላማም ይህንን ተፈፃሚ ማድረግ መሆኑን አመልክተዋል። ተቋማቱ በየተሰጣቸው ተልዕኮ ተቀናጅተው በትብብር በመስራት ለትምህርት ጥራት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለማድረግ ሚኒስቴሩ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡   የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የኮምፕሬሄንሲቭ ዩኒቨርሲቲዎች ማህበር ሰብሳቢ ድሪባ ኢቲቻ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የመማር ማስተማር ስራውን በላቀ መልኩ ለማከናወን በትብብር መስራት ወሳኝ መሆኑንና ማህበሩም ለእዚህ መቋቋሙን ገልጸዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ያላቸውን አቅም ተጠቅመው በትብብር በመስራት በሀገራዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተጨባጭ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ማህበሩ ይሰራል ብለዋል፡፡ በዚህም በመማር ማስተማር ሥራ፣ በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ሌሎች ዘርፎች ላይ በቅንጅት በመስራት ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት ትኩረት መደረጉን ነው ያስረዱት። የቀብሪደሀር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኢንጂነር አብድልፈታ አህመድ ጠቅላላ ጉባኤው በትብብርና በቅንጅት በመስራት በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለን ውስን ሀብት በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችል ነው ብለዋል።   ዩኒቨርሲቲው በመማር ማስተማር ስራው ብቁ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት የተሰጠውን ተልዕኮ በመወጣት ላይ መሆኑንም አንስተዋል። ኮምፕሬሄንሲቭ ዩኒቨርሲቲዎች በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት የበቁ ዜጎችን ማፍራት ተልዕኮ እንደተሰጣቸው የተናገሩት ደግሞ የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ቶፊቅ ጀማል (ዶ/ር) ናቸው፡፡   ዩኒቨርሲቲው በምርምር የተገኘና ቀደም ሲል በአካባቢው ያልተለመደ የተልባ ዝርያን ጨምሮ የኦቾሎኒ ሰብሎችን በአካባቢው እንዲላመድ በማድረግ ከሀገር ባለፈ ለኤክስፖርት ምርት አስተዋጾ ማድረጉንም አንስተዋል። የማህበሩ መቋቋም አንዱ ከሌላው እንዲማርና ከሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተሞክሮዎችን በማስፋት እንደሀገር በተለያዩ ዘርፎች የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ያስችላል ብለዋል፡፡ በጠቅላላ ጉባኤው በትምህርት ሚኒስቴር ኮምፕሬሄንሲቭ በሚል የተለዩት የ21 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶች መሳተፋቸው ታውቋል፡፡  
በኦሮሚያ ክልል ሴቶች እና ህጻናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመቀነስ ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረዋል
Dec 10, 2025 53
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 1/ 2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ሴቶች እና ህጻናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመቀነስ እና በሁሉም ዘርፎች ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ ስራዎች መጠናከራቸውን የክልሉ ሴቶችና የህፃናት ጉዳይ ቢሮ ገለጸ። በኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ የሚዘጋጀው 'ጉሚ በልበሎሚ' የተሰኘ የውይይት መርሃ ግብር ላይ የክልሉ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ እና የክልሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ሀላፊዎች ጋር ውይይት ተደርጓል። ቢሮው በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ በክልሉ 16 ዞኖች እና 14 ከተሞች ያካሄደውን የዳሰሳ ጥናት ለውይይቱ መነሻ አቅርቧል። በዳሰሳ ጥናቱ መሰረት፣ በተለይም ከለውጡ ወዲህ በክልሉ ሴቶችና ህፃናት መብቶችን ለመጠበቅ በተሰሩ ስራዎች ላይ ጥሩ መሻሻሎች መታየታቸው የተመለከተ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ችግሩ አሁንም እየተስተዋለ መሆኑ ተጠቅሷል። በተለይም በእነዚህ ወንጀሎች ላይ በቀበሌና በወረዳ ደረጃ በሚገኙ የመንግስት ሴክተር መስሪያ ቤቶች ተሳትፎ ዝቅተኛ መሆኑም ተነስቷል። የደሰሳ ጥናቱን አስመልክተው ማብራሪያ የሰጡት የክልሉ ሴቶችና የህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ፣ በክልሉ የሴቶችና ህፃናት መብቶችን ለመጠበቅ እና የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። በተለይም ከለውጡ ወዲህ መንግስት የሴቶችንና የህፃናትን መብቶች ለመጠበቅና በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመቀነስ ሴቶችን የማብቃት፣ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ወንጀል ፈጻሚዎችን በህግ ተጠያቂ የማድረግ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል። ቢሮው የሴቶችንና ህፃናትን መብቶች ለመጠበቅ፣ በሴቶችና በህፃናት ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ለመቀነስ እና ለተጎጂዎች አስፈላጊውን ድጋፍ ለመስጠት ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም አክለዋል። ከዚህ ጎን ለጎን የማህበረሰብ ተሳትፎ አስፈላጊ በመሆኑ ማህበረሰቡን በማሳተፍ ይህንን ችግር ለመግታት ተከታታይ ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል። በኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ቢሮ የምርመራ፣ ክትትል የስራ ሂደት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ዋንዳፍራሽ በበኩላቸው፥ በክልሉ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ ጉድለቶችን ለማረም በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህ ሂደት ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸውም አስረድተዋል።
በክልሉ የሚገኙ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች የተገልጋዩን ጊዜና ወጪ በመቆጠብ ጠቀሜታቸው የጎላ ነው 
Dec 10, 2025 50
ባሕር ዳር፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የሚገኙ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች የመደበኛ ፍትሕ ስርዓቱን ስራ ከማቃለል ባለፈ የተገልጋዩን ጊዜና ወጪ በመቆጠብ ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አለምአንተ አግደው ገለጹ። በአማራ ክልል ባሕላዊ ፍርድ ቤቶችን ስራ የሚያሳልጥ መመሪያ በቅርቡ ተግባራዊ እንደሚደረግም አቶ አለምአንተ አግደው ተናግረዋል። በክልሉ የባሕላዊ ፍርድ ቤቶች ማስተግበሪያ ጥናት፣ ትግበራ ዕቅድ እና ዕወቅና መስጫ መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በባሕርዳር ከተማ ውይይት ተደርጓል።   የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አለምአንተ አግደው እንዳመለከቱት፤ በክልሉ በርካታ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች አሉ። በዚህም የየአካባቢው ሕብረተሰብ እንደየነባራዊ ሁኔታው ግጭቶች ሲፈታባቸው የነበረ ቢሆንም በሕጋዊ ማዕቀፍ እውቅና ኑሯቸው በተደራጀ አግባብ ስራቸውን እንዲያከናውኑ አሰራር ሳይዘረጋ መቆየቱን አስታውሰዋል። አሁን ላይ የወጣውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ለባሕላዊ የግጭት መፍቻ ፍርድ ቤቶች እውቅና የሚሰጥ አሰራር መዘርጋቱንና ለዚሁ የሚሆን የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን ተናግረዋል። ባሕላዊ የግጭት አፈታት ስርዓቶች በቅርበት ለማሕበረሰቡ ተደራሽ በመሆን ዳኝነት በመስጠት፣ የመደበኛ ፍትሕ ስርዓቱን ስራ ከማቃለል ባለፈ የተገልጋዩን ጊዜና ወጪ በመቆጠብ ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በተደራጀና ሕጋዊ በሆነ አግባብ ስራቸውን እንዲያከናውኑ እንደሚደረግ ጠቁመው፤ የመመሪያው ዝግጅት በመጠናቀቁ በቅርቡም ወደ ስራ እንደሚገባ አስታውቀዋል። በክልሉ ሽምግልናን ጨምሮ አስራ አምስት ባሕላዊ የግጭት መፍቻ ስርዓቶች እንዳሉ በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው፤ ለእነዚሕ ስርዓቶች ሕጋዊ እውቅና በመስጠት ሕብረተሰቡን እንዲያገለግሉ ይደረጋል ብለዋል።   ባሕላዊ የግጭት መፍቻ ስርዓቶች እውቅና እንዲያገኙና በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆነው ግጭቶችን እንዲፈቱ መደረጉ የክልሉ ባሕላዊ የችግር መፍቻ ስርዓቶች እንዲሰፉ እድል የፈጠረ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አየለ አናውጤ(ዶ/ር) ናቸው። የባሕላዊ የግጭት መፍቻ ስርዓቶች ሕጋዊ እውቅና ተሰጥቷቸው እንዲሰሩ ማስቻል ባሕሉን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍም ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አንስተዋል። ክልል አቀፍ የሽምግልና መማክርት ጉባኤ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን ጠቀሰው፤ ይህም ባሕላዊ የሽምግልና ስርዓቱን በማሳለጥ ድርሻው የጎላ እንደሚሆን አስረድተዋል።
ኢኮኖሚ
ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ኮሚሽኑ
Dec 10, 2025 59
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- እየተከናወኑ ያሉ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአማራ ክልል አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ። በክልሉ የነበረውን ሥር የሰደደ የተረጂነት አስተሳሰብና ተግባር ለመቅረፍ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር ምክክሮች መደረጋቸውን የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሠርክአዲስ አታሌ ለኢዜአ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ከጠባቂነት መውጣትና እርስ በርስ የመደጋገፍ ዐቅምን ለማዳበር መግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመው፤ ይህን በይበልጥ ለማስፋትና ለማጠናከር ቀጣይነት ያላቸው ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል። እንደመንግስት ከሚከናወኑ ተግባራት ባለፈ መረዳትን ባህል እንዳሆን የሚያስችሉ እና ህብረተሰቡ የምግብ ሉዓላዊነቱን እንዲያረጋግጥ የማድረግ ስራ በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት። ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ ዐቅም ለመሸፈን ማምረት ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም ምክትል ኮሚሽነሯ አስገንዝበዋል። እስካሁን በተሠሩ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቁመው፤ በዚህ ከቀጠልን ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ መሸፈን የሚያስችል ዐቅም እናዳብራለን ሲሉም ተናግረዋል።
በምዕራብ ሸዋ ዞን የአፈር አሲዳማነትን በኖራ በማከም ከገብስ ልማት የተሻለ ምርት ይጠበቃል
Dec 10, 2025 77
አምቦ፤ ታህሳስ 01/2018 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ሸዋ ዞን በአፈር አሲዳማነት የተጠቃን መሬት በኖራ በማከም በተካሄደ የገብስ ልማት የተሻለ ምርት እንደሚጠበቅ የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። የኦሮሚያ ክልል እና የዞኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በዞኑ ወልመራ ወረዳ የገብስ ምርት አሰባሰብ ሂደትን ተመልክተዋል። በዚሁ ጊዜ የምዕራብ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ዲዳ ጉደታ እንደገለጹት፤ በዞኑ በተለይም በአፈር አሲዳማነት የተጠቃ መሬትን በኖራ በማከም በገብስ የማልማት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል። ባለፈው መኸር አዝመራ በገብስ የለማው ከዚህ በፊት እጅግ ዝቅተኛ ምርት የሚሰጥ በመሆኑ የዞኑ አርሶ አደሮችም መጠቀም አልቻሉም ነበር ብለዋል። መሬቱ በኖራ ከታከመ በኋላ ከአንድ ሄክታር መሬት እስከ 50 ኩንታል የገብስ ምርት እየተገኘ መሆኑን ጠቅሰው ይህም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ብቻ ሳይሆን ከውጪ የሚገባውን የቢራ ገብስ ለመተካት ያግዛል ነው ያሉት። በዚህም በዞኑ 48 ሺህ ሄክታር በቢራ ገብስ የለማ ሲሆን ከለማው መሬት ላይም 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚሰበሰብ ገልጸዋል። አርሶ አደሩ ለተመረተው ምርትም የገበያ ችግር እንዳይገጥመው ከዩኒየኖች እና ከኬኛ ቢቨሬጅ ጋር የገበያ ትስስር ስምምነት መፈጸማቸውንም አስረድተዋል። በወልመራ ወረዳም በተገባው ውል መሰረት በአርሶ አደሮች የቀረበ 578 ኩንታል የቢራ ገብስ ለዩኒየኖች መቅረቡን ጠቁመዋል። የወልመራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጋሪ በበኩላቸው፤ በወረዳው ከአርሶ አደሩ ጋር በቂ ውይይት ከተደረገ በኃላ በአሲድ የተጎዳውን መሬት በኖራ በማከም ወደ ምርት ማስገባት መቻሉን ተናግረዋል። ለመኸር አዝመራ ዝግጅትም 18 ሺህ ኩንታል ኖራ መከፋፈሉን ጠቅሰው ምርጥ ዘር እና የአፈር ማዳበሪያ በጊዜ በመቅረቡ የተሻለ ምርት እየተሰበሰበ ይገኛል ብለዋል። በወረዳው በመኸር አዝመራ 70 ሄክታር መሬት የቢራ ገብስ በማልማት ምርቱን በኮምባይነር ታግዞ እየተሰበሰበ መሆኑን ጠቅሰዋል። የወልመራ አርሶ አደሮችም በመኸር አዝመራ በኩታ ገጠም ያመረቱትን ገብስ ለገበያ እንዲያቀርቡ እድል መመቻቸቱ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያጎለብት ገልጸዋል።   ከወረዳው አርሶ አደሮች መካከል ደሲሳ ረጋሳ እንዳሉት፤ መሬታቸው በአሲድ የተጠቃ በመሆኑ የሚያገኙት ምርት ዝቅተኛ ነበር። ባለፈው ዓመት መሬቱን በኖራ ማከም በመቻላቸው ከአንድ ሄክታር መሬት 53 ኩንታል የገብስ ምርት ማግኘታቸውን አውስተዋል። መሬታቸውን በኖራ በማከምና ምርጥ ዘር እና ማዳበሪያ በአግባቡ በመጠቀማቸው የተሻለ ምርት ማግኘት መጀመራቸውን የገለጹት ደግሞ አርሶ አደር አሰፋ አንጋሱ ናቸው፡፡  
በኦሮሚያ ክልል 18 ሚሊዮን ኩንታል ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ይቀርባል
Dec 10, 2025 74
መቱ ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የቡና ምርትና ጥራትን በማስጠበቅ በምርት ዘመኑ 18 ሚሊዮን ኩንታል ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ እና የዞኑ አመራሮች በኢሉባቦር ዞን የተለያዩ ወረዳዎች እየተሰበሰበ የሚገኘውን የቡና ምርት ጥራትና አያያዝ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የቡናን ምርታማነትና ጥራትን በማሻሻል በገበያ ተወዳዳሪነቱን የተሻለ ለማድረግ ኢንሼቲቭ ተቀርጾለት እየተሰራ መሆኑ ነው የተመላከተው።   የቡና ምርትና ምርታማነቱን ለማሳደግም ያረጁ የቡና ዛፎችን ከመጎንደልና በአዲስ ከመተካት ባለፈ፣ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የቡና ችግኞችን ማዘጋጀት ላይም ትኩረት ተሰጥቷል። ለዚህም በቡና ልማትና ጥራት ፓኬጅ ላይ ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ ባለሙያዎችና አርሶ አደሮች የክህሎት ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉም ታውቋል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ እንዳሉት፤ በክልሉ የቡና ልማትና ጥራትን በማስጠበቅ በምርት ዘመኑ 18 ሚሊዮን ኩንታል ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው። የቡና ጥራትን ለማረጋገጥ ቀይ እሸት ቡና በመልቀምና በአልጋ ላይ በማድረቅ በክምችትና በማጓጓዝ ብክለት እንዳይከሰት ክትትል እየተደረገ መሆኑን አንስተው፤ በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 8 ሚሊዮን ኩንታል መሰብሰቡን ተናግረዋል።   ከቡና የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግም ከቡና ልማት እስከ ምርት አሰባሰብ ድረስ ለምርት ጥራት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት። በኢሉባቦር ዞን በቡና ከለማው 342 ሺህ ሔክታር መሬት በቡና መልማቱንና ከዚህም 74 ሺህ ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ‎አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ ናቸው። በዞኑ በቡና ንግድ ስራ ላይ 22 ማሕበራት መሰማራታቸውንና ለጥራቱም ትኩረት እንዲሰጡ ግንዛቤ እንደተሰጣቸውም አስረድተዋል።   የቡና ምርት ጥራትን በማስጠበቅ የአምራቾች እና አቅራቢዎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታውን ለማሳደግ ህገወጥ ንግድን መቆጣጠር ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አቶ እንዳልካቸው አንስተዋል። በዞኑ የመቱ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ደሳለኝ ተፈሪና አቶ ገመቹ ተካ በበኩላቸው ቀይ ቡናን በመልቀምና በአልጋ ላይ በማድረቅ ለገበያ ለማቅረብ እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
በክልሉ በተከታታይ እየተተገበረ የሚገኘው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው
Dec 10, 2025 71
አምቦ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል በተከታታይ እየተተገበረ የሚገኘው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መምጣቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በዞኑ በወልመራ ወረዳ በበጋ መስኖ የሚለማ ስንዴ የዘር መዝራት መርሃ ግብር የክልሉ፣ የዞንና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተካሄዷል።   የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደጀኔ ሂርጳ እንዳሉት፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከታታይ እየተተገበረ የሚገኘው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው። ዘንድሮም በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች አርሶ አደሩ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት መሳተፍ እንዲችል የግብዓት፣ የቴክኖሎጂ እና የባለሙያ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።   በምዕራብ ሸዋ ዞንም አርሶ አደሩ በኩታ ገጠም ተደራጅቶ የበጋ መስኖ ስንዴን ማልማት መጀመሩን ገልጸው በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። የምዕራብ ሸዋ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተረፈ አራርሳ በበኩላቸው፤ በዞኑ በበጋው መስኖ 400 ሺህ ሔክታር መሬት ይለማል ብለዋል።   በእስካሁኑ ሂደትም 200 ሺህ ሄክታር መሬት የማሳ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸው ልማቱን ስኬታማ ለማድረግ የግብዓት አቅርቦት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል። የወልመራ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና እና መሬት አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጎሳዬ ሂርጳ፤ የወረዳው አርሶ አደሮች የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴን እየተለማመዱ መምጣታቸውን ተናግረዋል።   በዚህም በወረዳው ምርትና ምርታማነት እያደገ መምጣቱን ገልጸው በዘንድሮ በጋ ወራት 25 ሺህ ሄክታር መሬት በስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን 21 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ገልጸዋል፡፡ የወረዳው አርሶ አደሮች ባለፉት ዓመታት ስንዴን በበጋ መስኖ በማልማት ተጠቃሚነታቸው እያደገ፤ ኑሯቸውም እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግረዋል። አርሶ አደር ድሪባ በቀለ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር በጋራ በመሆን በኩታ ገጠም የበጋ ስንዴ እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል።   የበጋ ስንዴን በኩታ ገጠም ማልማት ሳይጀመሩ በፊት በሄክታር ትንሽ ምርት ሲያገኙ መቆየታቸውን አንስተው ዘንድሮ ከሄክታር 30 ኩንታል ስንዴ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በኩታ ገጠም ልማቱም የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ባለሙያዎች ከመሬት ዝግጅት ጀምሮ እገዛ እያደረጉላቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል። ሌላው አርሶ አደር ባዩ ጐንፋ፤ በተያዘው በጋ በመስኖ የተሻለ ምርት ለማግኘት የሚያስችላቸውን ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን በመግለፅ በሙሉ አቅም ወደ ስራ መግባታቸውን አስረድተዋል።   በበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱም ኑሯቸው እየተሻሻለ፤ ተጠቃሚነታቸውም እያደገ በመምጣቱ በተያዘው በጋም የተሻለ ምርት ለማግኘት ዘር መዝራት መጀመራቸውን ገልጸዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በዲጂታል ክፍያ ያስመዘገበችው አስደናቂ ስኬት ተጨማሪ ግቦችን ለማሳካት መሠረት የሚሆኑ ናቸው
Dec 10, 2025 54
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 1/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በዲጂታል ክፍያ ያስመዘገበችው አስደናቂ ስኬት ተጨማሪ ግቦችን ለማሳካት መሠረት የሚሆኑ ናቸው ሲሉ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ። ሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል።   በጉባኤው ማጠናቀቂያ ንግግር ያደረጉት የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል ክፍያ ዘርፍ እያስመዘገበች ያለችው ዕድገት አስደናቂ ነው። አሁን ላይ አብዛኛው ዜጋ ከፍተኛ መጠን ያለው ጥሬ ገንዘብ መያዝ አቁሟል ያሉት ገዥው፤ ኢትዮጵያውያን የዲጂታላይዜሽን እና የዳታ ሽግግርን በፍጥነት እየተላመዱ እንደሚገኙም አስረድተዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በተዘረጋው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በየዓመቱ ከ18 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር መከናወኑን ተናግረዋል። ይህን የገንዘብ ዝውውር በጥሬ ገንዘብ ቢከናወን ከፍተኛ ወጪና መጨናነቅ ይፈጥር እንደነበር ጠቁመው፤ ይህ ስኬት ከጥቂት ዓመታት በፊት ፈጽሞ የማይታሰብ እንደነበር ጠቅሰዋል። የመሠረተ ልማትን ለማስፋፋት የተሰጠው ትኩረት ዋነኛ የስኬቱ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥትን ወደ ዲጂታል ግብይት እና የገንዘብ ዝውውር አገልግሎት ለማሸጋገር የሰጠው ትኩረት ለተመዘገበው ውጤት ትልቅ እርምጃ መሆኑን ጠቅሰው፤ በትክክል የታሰበበት፣ በጥንቃቄ የተቀረጸና ተግባራዊ የተደረገ የስትራቴጂ ውጤት ስለመሆኑም ጠቁመዋል። እስካሁን የተገኘውን ውጤት ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሰራ ጠቁመው፤ ውጤቱ የሚያዘናጋ ሳይሆን መስፈንጠሪያ ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል። በቀጣይ የዲጂታል ባንኪንግ ተጠቃሚዎችን እምነት ለማሳደግ እና የሥርዓቱን ደኅንነት ይበልጥ ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ጠቅሰው፤ በገጠርና በከተማ ያለውን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልዩነት ለመቀነስ ይሠራል ብለዋል። እንዲሁም የፈጠራ ሥራዎችን በበቂ ሀብት የመደገፍ ሥራዎች ወሳኝ በመሆናቸው በልዩ ትኩረት ይሠራል ብለዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በቁርጠኝነት ሠርታ ያስመዘገበቻቸው ትላልቅ ውጤቶች በቀጣዮቹ ዓመታት ለማሳካት ያስቀመጠቻቸውን ግቦች ለማሳካት ትልቅ መሠረት የሚሆኑ ናቸውም ብለዋል። ኢትዮጵያ የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን ለመገንባት ትክክለኛ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመቅረፅ ትክክለኛውን እርምጃ መውሰዷንም ገልጸዋል። ሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ የመረጃ መሠረተ ልማትን ለማጠናከር፣ የዲጂታል ክፍያ እና ሰፋፊ የዲጂታል ስትራቴጂዎችን ለማስገንዘብ ሰፊ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት መንግስት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም በርካታ ኢንቨስትመንት መከናወኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዲጂታል ክፍያ ዘርፍ እንዲስፋፋ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በቀጣይ ትኩረት ከሚሰጣቸው ተግባራት መካከል የመረጃ ሉዓላዊነት ጉዳይን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በብዙ መልኩ ኢንቨስት እያደረገች እንደምትገኝም አስረድተዋል። የኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስና የክፍያ ሥርዓት በፈጣን የዕድገት ጎዳና ላይ እንደምትገኝም ጠቁመዋል። ከ2026 -2030 የሚተገበረው ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ በሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ይፋ መደረጉን ይታወቃል።  
የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ልማት መርሃ ግብር እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኅይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት ያለመ ነው  
Dec 10, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ልማት መርሃ ግብር ከኢኮኖሚው ጋር አብሮ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኅይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት ያለመ መሆኑን የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሽፈራው ተሊላ ገለጹ። የመጀመሪያው ብሔራዊ የኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር ሚና እና ኃላፊነት የተቋም ትግበራ አውደ ጥናት የምክክር መድረክ ሁለተኛ ቀን ቀጥሏል።   የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኅይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሽፈራው ተሊላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የኒውክሊየር ኃይል ተፈጥሮ ለአንድ ሀገር ዘላቂ ልማት እና እድገት ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ የምትከተለው አረንጓዴ ኢኮኖሚ መሆኑን ገልጸው፤ የኢንዱስትሪዎቿ ቁጥር እና ዓይነት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ወደ ኋላ እንዳይመለስ የኃይል ምንጭን አስቀድሞ ማዘጋጀት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሰላማዊ የኒውክሊየር ልማት መርሃ ግብር እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ምላሽ መስጠት የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አብዱረዛቅ ኡመር በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ከአካባቢ ጥበቃ ጋር የተስማማ በቂ እና አስተማማኝ ኃይል ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ ወደ ፊት መራመድ እንደምትፈልግ ተናግረዋል።   የኢትዮጵያን ሰላማዊ የኒውክሌር ኃይል አማራጭ የሀገሪቱን የልማት ትልሞች የሚያሳካ መሆኑን ጠቁመዋል። በመካሄድ ላይ ባለው ዓውደ ጥናት የተለያዩ ሀገራት ልምድ እና ተሞክሮዎች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም አንድ ሰላማዊ የኒውክሊየር መሰረተ ልማት ለማቋቋም መከናወን ባለባቸው ተግባራት ላይ ግንዛቤ እየተፈጠረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።  
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራ በይፋ ተጀመረ
Dec 10, 2025 76
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ):- የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራን ዛሬ በጋራ ማስጀመራቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቁ። ሁለቱ ተቋማት ባወጡት የጋራ መግለጫ ፋይዳ ዲጂታል የማንነት መረጃ ከሁሉም ባንኮች የደንበኞች ባንክ ሂሳብ ቁጥር ጋር የማጣመር (Harmonization) ስራን በይፋ መጀመሩን ገልጸዋል። ይህ የመረጃ ሥርዓቶችን የማጣመር ስራ ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ገንዘብ ማስተላለፍ እንዲችሉ፣ በሀሰተኛ ሰነድ የራሳቸውን ሂሳብ ሌሎች ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ፣ በቀላሉ የብድር አገልግሎትን ማግኘት እንዲችሉ እና በአንድ ፋይዳ መታወቂያ የሁሉንም ባንክ ሂሳብ መጠቀም እንዲያስችላቸው ተመላክቷል። ባንኮች በዚህ መረጃ ጥምረት የደንበኞቻቸውን ትክክለኛ እና ወቅታዊ መረጃን እንዲያገኙ፣ በሀሰተኛ ማንነት የሚከሰት የገንዘብ መጭበርበርን ከመከላከል ባለፈ ለፋይናንስ ሴክተር ዲጂታል ትግበራ ቁልፍ የዲጂታል መሰረተ ልማት ሆኖ እንደሚያገለግል መግለጫው ያትታል። ይህን የባንክ ሂሳብ ቁጥር ከፋይዳ መረጃ ጋር ለማጣመር ደንበኞች ወደ ባንክ ቅርንጫፎቻቸው በአካል በመሔድ ወይም ኦንላይን(ባንኩ በሚያስቀምጠው አሰራር መሰረት) የፋይዳ ተለዋጭ ቁጥር (16 አሀዝ-FAN Number) በማቅረብ ማከናወን ይችላሉ። ደንበኞች በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ማለትም እስከ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የባንክ ሂሳባቸውን ከፋይዳ መረጃ ጋር እንዲያጣምሩ ብሔራዊ ባንክ አሳስቧል። ለፋይዳ ያልተመዘገበ ማንኛውም የባንክ ደንበኛ በቅድሚያ በአቅራቢያው በሚያገኘው የፋይዳ ምዝገባ ጣቢያ በመሄድ መመዝገብ እንዳለበትና ባንኮች በዚህ ሂደት ደንበኞች መጉላላት እንዳያጋጥማቸው አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ በመፈፀም ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል። በሁሉም ባንኮች አዲስ ሂሳብ መክፈት(New Account Opening) (በ “VeriFayda 2” እንዲጀመር፣ እንዲሁም ነባር ሂሳቦችን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር (Existing Account Harmonization) ትግበራም በ “VeriFayda 2” ተግባራዊ የሚደረግበት የጊዜ ሰሌዳ ወጥቶ ለሁሉም ባንኮች ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም መሰራጨቱ በመግለጫው ላይ ሰፍሯል። ቀደም ሲል ሁሉም ባንኮች አዲስ ሂሳብ ለመክፈት የ VeriFayda 1 ስርዓትን ሲጠቀሙ መቆየታቸውም ተመላክቷል፡፡ ከዚህ በኋላ ባንኮች ይበልጥ ዘመናዊና የተቀናጀ ወደ ሆነ ስርዓት “VeriFayda 2” (በኢቲስዊች - EthSwitch በh-A eKYC Service) የማሸጋገር ሥራን በተሳካ ሁኔታ እንዲያከናውኑ የፕሮግራሙና የኢቲስዊች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ለባንክ ተቋማት የቴክኒክ ድጋፍ እና ክትትል እያደረጉ ይገኛል። በቀጣይም የቴክኒክ ድጋፉ እንደሚቀጥል ባንኩ አስታውቋል። በተመሳሳይ ሁሉም ባንኮች ለደንበኞቻቸው አዲስ የባንክ ሂሳብ ለመክፈትም ሆነ ከነባር ሂሳብ ጋር የማጣመር ስራን በመስራት ከVeriFayda 1 (old eKYC) ሙሉ በሙሉ ወደ VeriFayda 2 (new eKYC Service) መሸጋገር እንደሚኖርባቸው ባንኩ አሳስቧል። ይህንን ተከትሎ ቀደም ሲል ባንኮች ሲጠቀሙበት የነበረው የ VeriFayda 1 (eKYC Service) ስርዓት አገልግሎት መስጠት እንደሚያቆምም አመልክቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ይህን የማጣመር ስራ በፍጥነት ወደ ትግበራ ማስገባታቸው ለፋይናንስ ዘርፉ ብቻ ሳይሆን ሀገሪቱ ወደ ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ላይ ትልቁን ሚና እንደሚጫወት ተመላክቷል።
የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ዝርያን ለማሻሻል የተጀመሩ ውጤታማ ተግባራት ይጠናከራሉ
Dec 10, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ዝርያን ለማሻሻል የተጀመሩ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዳኛቸው በየነ (ዶ/ር) ገለጹ። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በግብርናው ዘርፍ ያሉ እምቅ ሀብቶችን ጥቅም ላይ ለማዋል የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ሲሆን የእንስሳት ምርታማነትን ለማሳደግ የተሠሩ ስራዎችም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በተለይም የሌማት ትሩፋት ተግባራዊ ከሆነ ወዲህ የእንስሳት ምርታማነት በተጨባጭ ያደገ ሲሆን የበርካቶችን ህይወት በመለወጥም ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጠ እንደሚገኝ ነው የተመላከተው፡፡ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዳኛቸው በየነ (ዶ/ር)፤ ኢንስቲትዩት የዳልጋ ከብቶችን ጨምሮ የእንስሳት ሃብቶች ላይ የዝርያ ማሻሻያዎችን በመሥራት የእንስሳት ተዋጽኦ አቅርቦት እንዲጨምር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል፡፡   በተለይም ከፍተኛ ምርት መስጠት የሚችሉ የውጭ ዝርያዎችን በሀገር ውስጥ ካሉ ላሞችና ጊደሮች ጋር በማዳቀል የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸው እንዲበራከቱ እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ ይህም አርብቶና አርሶ አደሩ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን እንዲያገኙ በማድረግ ከእንስሳቱ የሚያገኙት ተዋጽኦ በመጠንና በጥራት እያደገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚህም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተግባራዊ የተደረገው የሌማት ትሩፋት ዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡   በቀጣይም በሰው ሰራሽ ዘዴ የማዳቀል፣ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን የመጠቅምና ባለሙያዎች ተጨማሪ ክህሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል፡፡ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም፤ ኢንስቲትዩቱ የሚያመርተውን የፈሳሽ ናይትሮጂን ደህንነቱ ተጠብቆ ለእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ተግባር እንዲውል እየተደረገ መሆኑንም አክለዋል። ኢንስቲትዩቱ በበጀት ዓመቱ 4 ነጥብ 9 ሚሊዮን ላሞችና ጊደሮችን ለማዳቀል የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የሆለታ እንስሳት ልማት ማዕከል ኃላፊ አራርሳ ዱጉማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ኢትዮጵያ በእንስሳት ዘርፉ ላይ ያላትን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   በዚህም ዝርያዎችን የማሻሻል፣ የእንስሳት አዳቃይ ቴክኒሺያኖችን የማሰልጠንና የተቀነባበረ መኖ ማምረትን ጨምሮ ሌሎችንም ስራዎች እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ማዕከሉ የተሻሻሉ ጊደሮችን ለተጠቃሚዎች ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
ስፖርት
ኢትዮጵያ መድን ከሸገር ከተማ ጋር ተስተካካይ ጨዋታውን ዛሬ ያደርጋል
Dec 10, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ መድን ከሸገር ከተማ ይጫወታሉ። ጨዋታው ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይካሄዳል። ኢትዮጵያ መድን በሊጉ ካደረጋቸው ስምንት ጨዋታዎች መካከል ሁለቱን ሲያሽንፍ ሶስት ጊዜ ደግሞ ተሸንፏል። በቀሪ ሶስት ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ ስድስት ግቦችን ሲያስቆጥር ሰባት ጎሎችን አስተናግዷል። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በዘጠኝ ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። ሸገር ከተማ በበኩሉ በሊጉ ካከናወናቸው ስምንት ጨዋታዎች መካከል በሶስቱ ድል ሲቀናው ሁለት ጊዜ ተሸንፏል። ሶስት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። ዘጠኝ ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያገናኝ ሰባት ግቦች ተቆጥረውበታል። አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በ12 ነጥብ 10ኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታው ኢትዮጵያ መድን ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ ሸገር ከተማ ደግሞ በአሸናፊነቱ ለመቀጠል የሚያደርጉት ነው። መርሃ ግብሩ ኢትዮጵያ መድን በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ከግብጹ ፒራሚድስ ጋር በነበረው የማጣሪያ ጨዋታ ምክንያት የተራዘመ መሆኑን የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል።
ተጠባቂው የሪያል ማድሪድ እና የማንችስተር ሲቲ የሻምፒዮንስ ሊግ ፍልሚያ 
Dec 10, 2025 81
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ዘጠኝ ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት 5 ሰዓት ላይ ሪያል ማድሪድ እና ማንችስተር በበርናባው ስታዲየም የሚያገናኘው ጨዋታ የእግር ኳስ ቤተሰቡን ትኩረት ስቧል። ሪያል ማድሪድ በ12 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ማንችስተር ሲቲ በ10 ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሁለቱ ክለቦች በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊጉ ሲገናኙ የአሁኑ ለ15ኛ ጊዜ ነው። ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 14 ጨዋታዎች ማንችስተር ሲቲ አምስት ጊዜ ሲያሸንፍ ሪያል ማድሪድ አራት ጊዜ ድል ቀንቶታል። በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። ሁለቱም ቡድኖች በጨዋታዎቹ ላይ በተመሳሳይ 24 ግቦችን አስቆጥረዋል።   ቡድኖቹ በሻምፒዮንስ ሊጉ ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት እ.አ.አ በ2024/25 የውድድር ዓመት ነው። በጥሎ ማለፉ ተገናኝተው ሪያል ማድሪድ ማንችስተር ሲቲን 3 ለ 1 አሸንፏል። የስፔኑ ቡድን 15 ጊዜ ውድድሩን በማሸነፍ በስኬት ያሸበረቀ ታሪክ አለው። ማንችስተር ሲቲ አንድ ጊዜ ዋንጫ አንስቷል። ሪያል ማድሪድ እና ማንችስተር ሲቲ ባለፉት ዓመታት በአውሮፓ መድረክ እያደረጉት ያለው ፉክክር የዛሬውን ጨዋታ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጎታል። በሌሎች መርሃ ግብሮች ክለብ ብሩዥ ከሊግ ፎርማቱ መሪ አርሰናል፣ አትሌቲኮ ቢልባኦ ከወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ፒኤስጂ፣ ጁቬንቱስ ከፓፎስ፣ ቤኔፊካ ከናፖሊ፣ ባየር ሌቨርኩሰን ከኒውካስትል ዩናይትድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ከቦዶ ግሊምት በተመሳሳይ ከምሽቱ 5 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ካራባግ ከአያክስ እና ቪያሪያል ከኮፐንሃገን ይጫወታሉ።
ሊቨርፑል ኢንተር ሚላንን አሸነፈ
Dec 10, 2025 92
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 30/2018(ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሊግ ሻምፒዮንስ ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ሊቨርፑል ኢንተር ሚላንን 1 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በጁሴፔ ሜኤዛ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዶምኒክ ስቦዝላይ በ88ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል። ጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር ተደርጎበታል። ውጤቱን ተከትሎ ሊቨርፑል በ12 ነጥብ ደረጃውን ወደ ስምንት ከፍ አድርጓል። ኢንተር ሚላን በተመሳሳይ 12 ነጥብ በግብ ክፍያ በልጦ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በሌላኛው ጨዋታ አትላንታ ቼልሲን 2 ለ 1 አሸንፏል። ጂያንሉካ ስካማካ እና ቻርልስ ዲ ኬቴላሬ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጆአኦ ፔድሮ ለቼልሲ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ቶተንሃም ሆትስፐርስ ስላቪያ ፕራግን 3 ለ 0 አሸንፏል። መሐመድ ኩዱስ፣ ዣቪ ሲመንስ እና የስላቪያ ፕራጉ ዴቫድ ዚማ በራሱ ላይ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ጁል ኩንዴ ባስቆጠራቸው ግቦች ባርሴሎና ከመመራት ተነስቶ ኢንትራክት ፍራንክፈርትን 2 ለ 1 አሸንፏል። አንስጋር ናውፍ ለጀርመኑ ቡድን ብቸኛውን ጎል ከመረብ ጋር አገናኝቷል። በሌሎች ጨዋታዎች አትሌቲኮ ማድሪድ ፒኤስቪ አይንድሆቨንን እና ማርሴይ ዩኒየን ሴንት ጊሎይስን በተመሳሳይ 3 ለ 2 ሲያሸንፉ ሞናኮ ጋላታሳራይን 1 ለ 0 ረቷል። ዛሬ አስቀድመው በተደረጉ ጨዋታዎች ባየር ሙኒክ ስፖርቲንግ ሊዝበንን 3 ለ 1፣ ኦሎምፒያኮስ ካይራት አልማቲን 1 ለ 0 አሸንፈዋል።
አካባቢ ጥበቃ
በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ዕድልን ለማስፋፋት የግሉ ዘርፍ ሚና የጎላ ነው
Dec 10, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ የስራ ዕድልን ለማስፋፋት የግሉ ዘርፍ ሚና የጎላ መሆኑን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ”አረንጓዴ ስራዎች የተሻለ ነገ” በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ፎረምና ባዛር ማካሄድ ጀምሯል።   የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ መንግሥት በመደመር እሳቤ በኢኮኖሚ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልዱ ለማስረከብ በርካታ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል። ባለሃብቶችና ኢንተርፕራይዞች በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዙሪያ ያላቸውን ፈጠራና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያሳድጉ ፣ በተለይም በታዳሽ ሃይል ላይ የሚውል ካፒታል ፈሰስ ማድረግ፣ የኢኮኖሚ ኢኒሸቲቮችን ማገዝና ግብርናውን ማዘመን ላይ እንዲሳተፉ አሳስበዋል፡፡፡ ከነዚህ መካከል የሀገሪቱን የአየር ንብረት ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስራ ተጠቃሽ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   የኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግር በግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት፣ በአረንጓዴ ፈጠራ፣ ፋይናንስና ኢንተርፕርነርሺፕ ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ በአረንጓዴ የኢኮኖሚ ዘርፍ የሚፈጠር የስራ ዕድል ለኢትዮጵያ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ተግባሩ ከስራ፣ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ጋር ከተጣመረ ዘርፉን በፍጥነት ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚን በመጠቀም የስራ እድል ፈጠራን ለማስፋፋት የያዘቸውን ግብ እንድታሳካ አጋር አካላት የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።   በኢትዮጵያ የስዊድን ኤምባሲ ከፍተኛ የፕሮግራም ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኒኮላ ኤሪክሰን አረንጓዴ የስራ ዕድል ፈጠራ ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችውን ሽግግር ለማገዝና የማይበገርና የተሰባጠረ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ ታዳሽ የሃይል አቅርቦትና ትራንስፖርት፣የአየር ብክለት ልቀት ቅነሳ፣የቆሻሻ አወጋገድ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ በማደግ ላይ የሚገኙ አማራጮች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ይህንን እውን ማድረግ የሚችል በእውቀት የበለጸገና ጠንካራ ወጣት ሃይል አላት ብለዋል፡፡    
በምዕራብ ጎንደር ዞን የበጋ ወቅት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ተጀመረ
Dec 10, 2025 69
ገንዳውሃ፤ ታህሳስ 1/2018(ኦዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን በተለያዩ ተፋሰሶች የበጋ ወቅት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ መጀመሩን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ ዛሬ በተጀመረው በዚሁ ሥራ ላይ የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የፌዴራል ፖሊስና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉ ሲሆን፤ ሥራው ለ30 ቀናት እንደሚቆይ ተነግሯል ፡፡ የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በዞኑ በአራት ወረዳዎችና ሶስት ከተማ አስተዳደሮች በሚተገበረው የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ 2ሺ 300 ሄክታር የተጎዳ መሬት ይለማል። ከዚህ ውስጥ በዛሬው ማስጀመሪያ ፕሮግራም በተለያዩ ቀበሌዎች 110 ተፋሰሶች ላይ መከናወኑን አንስተዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ተግባር በወል መሬቶችና በግል ይዞታዎች የሚሰራ ሲሆን፤በዚህም የውሃ እቀባ፣ እርከን ሥራና ሌሎች ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል። በዘመቻ በሚካሄደው በዚህ የልማት ሥራ ከ36 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን ለማሳተፍ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አስረድተዋል። አርሶ አደሮቹ የተፋሰስ ልማት ሥራዎቹን ቀጣይነት ያለው ቁጥጥርና ክትትል በማድረግ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸውን ለማጉላት በተለየው መሬት ላይ ዕፅዋቶች እንዲያለሙ እንደሚደረግ ገልጸዋል። በሰሜን ምዕራብ ዕዝ የ504ኛ ኮር ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ቾምቤ ወርቁ በበኩላቸው፤ ሰራዊቱ ሰላምና ዳር ድንበርን ከማስከበር በተጨማሪ በልማት ሥራዎች በመሳተፍ ለሀገር እድገት የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። በበጋ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በተከናወነበት ሥፍራ ክረምት ላይ ችግኝ በመትከል የሚሳተፉ መሆኑንም ጠቁመዋል። በዞኑ የገንዳውኃ ዙሪያ አርሶ አደር አየነው ያሲን በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ዓመታት በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ላይ ተሳትፈው መልካም ውጤት በማየታቸው በዚህ ዓመት ሥራውን አጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታት በወል መሬት ላይ በተከናወነው እርከንና ችግኝ ተከላ ልማት አፈሩ ተሸርሽሮ ከጥቅም ውጭ የነበረ ስፍራ አገግሞ ለከብት መኖና የከርሰ ምድር ውሃን በማጎልበት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸውም አውስተዋል።   በበጋ የአፈርና ውሃ የጥበቃ ሥራዎች የለሙ ተፋሰሶች ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው የገለጹት ሌላኛው አርሶ አደር የሱፍ ዳምጤ ናቸው።  
ኢትዮጵያ ኮፕ- 32 እንድታስተናግድ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የሚያስችሉ ስራዎች ውጤታማነትን የሚያመላክት ነው
Dec 10, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤን (ኮፕ- 32) እንድታስተናግድ መመረጧ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም የሚያስችሉ ስራዎች ውጤታማነትን የሚያመላክት መሆኑን በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ጉዳይ ፈጻሚ ፈርዲናንድ ቮን ዌይህ (ዶ/ር) ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአካባቢ ስነ-ምኅዳር ደኅንነት በማስጠበቅ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ በብራዚል ቤለም በተካሄደው የዓለም የአየር ንብረት (COP-30) ጉባኤ ላይ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት (COP-32) ጉባኤ ለማስተናገድ መመረጧ ይታወቃል። በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ጉዳይ ፈጻሚ ፈርዲናንድ ቮን ዌይህ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት በኢትዮጵያ በሀይድሮ የኤሌትሪክ ሀይል፣ አረንጓዴ አሻራና ሌሎች በአረንጓዴ ልማት በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም እያከናወነች የምትገኘው ተግባር ችግሩን ለመከላከል ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያመላክትም ተናግረዋል። በኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ ፣ በታዳሽ ሀይል እና በደን ልማት የተሰሩ ውጤታማ ስራዎች ኢትዮጵያ የኮፕ-32 ጉባኤን እንድታስተናግድ ለመመረጧ አስተዋጽኦ ማድረጉን ገልጸዋል። በሀገሪቱና በዓለም አቀፍ ደረጃ በተካሄዱ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤዎች ኢትዮጵያ የነበራት ጉልህ ተሳትፎ ለመመረጧ ካገዟት መስፈርቶቹ መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል። በጀርመን የልማት እቅድ የግብርና ዘርፍ ዋና ምስሶ መሆኑን ገልጸው፤ ለዘርፉ ውጤታማነት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚከናወኑ ስራዎች ትኩረት ከሚደረግባቸው ስራዎች መካከል እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። ጀርመን በኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን እየደገፈች እንደምትገኝ ገልጸው፤ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ረቂቅ አዋጁ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስራዎችን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ጉልህ ጠቀሜታ ይኖረዋል 
Dec 5, 2025 287
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 26/2018(ኢዜአ)፦የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ የሀገሪቱን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስራዎች የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ ገለጹ። በሕዝበ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት እና የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ይፋዊ ውይይት መድረክ አካሂደዋል።   በምክር ቤቱ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ በዚሁ ወቅት፤ የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ በተለያዩ አሰራሮች ላይ መኖሩን ጠቅሰዋል፡፡ አንድ ወጥ በሆነ አሰራር፣ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችና ሀገሪቱ ከደረሰችበት ደረጃ ጋር በተጣጣመ መልኩ ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱ አስፈላጊ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የሀገሪቱን የበለጸገ የስነ ምህዳር ሀብት ዘላቂ በሆነ ወጥ አሰራር ለማጠናከር የአገልግሎት ክፍያ ስርዓቱ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የደን ልማቶች የግብርና ምርታማነትን በማጎልበት አረንጓዴ ልማቶችን የበለጠ ውጤታማ ያደርጋል ብለዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የተፈጥሮ ሀብቶችን ጥበቃና እንክብካቤን በማጠናከር አካባቢ ላይ የሚደርሰውን ጉዳትና የህብረተሰቡን ተጋላጭነት መቀነስ አስፈላጊ ነው።   ረቂቅ አዋጁ ለመጀመሪያ ጊዜ መዘጋጀቱን ገልጸው፤ የተለያዩ ማህበረሰብ ክፍሎች አካባቢያቸውን በመጠበቃቸው ለአገልግሎታቸው ክፍያ እንዲያገኙ የሚያደርግ የማበረታቻ ስርዓት የሚዘረጋ ነው ብለዋል። ስነ ምህዳር ላይ ጉዳት የሚያደርሱ እንቅስቃሴዎችን ለመከላከል የአካባቢን ጥበቃ በዘላቂነት የሚያበረታታ ሂደትን የሚፈጥር አዋጅ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በውይይቱ ላይ የተገኙ ባለ ድርሻ አካላት የስነ ምህዳር አገልግሎት አቅራቢዎች፣ ረቂቅ አዋጁ ላይ መካተት የሚገባቸውን ጉዳዮች፣ ግልጽነትን የሚጠይቁና ከትርጉም ጋር በተያያዘ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ለሊሴ ነሜ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤በረቂቅ አዋጁ የስነ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ላይ የማህበረሰቡና የባለ ድርሻ አካላት ተጠቃሚነት፣ ተሳታፊነትና ፍትሃዊነት በግልጽ መቀመጡን ተናግረዋል። አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ የመንግስት ተቋማትና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት አገልግሎት አቅራቢዎች ይሆናሉ ብለዋል። ከግብርናና ከደን ልማት ጋር ተያይዞ የስነ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ አስገዳጅ የሆነባቸው አዋጆች መኖራቸውን ጠቅሰው ረቂቅ አዋጁ የክፍያ ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የፌደራልና የክልል ባለ ድርሻ አካላትን ሚና እና ሀላፊነትም በግልጽ አስቀምጧል ብለዋል።   በምክር ቤቱ የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር)፤ በረቂቅ አዋጁ ላይ አሻሚ ትርጉም የሚሰጡ፣ ግልጽነት የጎደላቸው ጉዳዮች ተሻሽለው ጠንካራ አዋጅ እንዲወጣ በጋራ እንሰራለን ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል
Dec 4, 2025 393
አዲስ አበባ፤ ህዳር 25/2018(ኢዜአ)፦ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ ተከናውኗል።   በዕውቅና መርሃ ገብሩ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትአለም መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዘርፍ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ሽልማቱ ለአፍሪካ ጋዜጠኝነት፣ ብሮድካስት ሚዲያ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ዘገባዎች እውቅና የሰጠ ነው። በአፍሪካ ሚዲያ ምህዳርን በመቅረጽ ሚናቸውን የተወጡ ጋዜጠኞች ተሸልመዋል። ምርጥ የዜና ዘገባ፣ ምርጥ ቃለ መጠይቅ፣ ምርጥ ዶክመንተሪ፣ ምርጥ ወቅታዊ ፕሮግራም፣ ምርጥ አፍሪካ ተኮር የመዝናኛ ፕሮግራምና ምርጥ የቪዲዮ ፕሮዳክሽን በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ እና ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው።   አፍሪካ ተኮር ምርጥ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ምርጥ የወቅታዊ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ እና ምርጥ አጭር የማህበራዊ ሚዲያ ተንቀሳቃሽ ምስል የማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የተሰጠባቸው ዘርፎች ናቸው። ሁሉም እጩዎች 2000 ዶላር ሽልማት ያገኙ ሲሆን በእያንዳንዱ ዘርፍ ያሸነፉ ተወዳዳሪዎች የስድስት ሺህ ዶላር ሽልማት አግኝተዋል። የምርጦች ምርጥ የይዘት ፈጣሪዎች አሸናፊም "The Golden Alkebulan" የተሰኘ ልዩ በወርቅ የተለበጠ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በሽልማቱ ላይ ከ40 ሀገራት በላይ የተወጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ከ800 በላይ ስራዎችን ማቅረባቸውን ተገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ፣ የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽንና የሩስያው አር ቲ ሚዲያ የሽልማቱ አጋር ናቸው።
ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው - የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች
Dec 1, 2025 387
አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ ነው ሲሉየምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ገለጹ። የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት በመቀየር ትልቅ ሚና የሚወጣ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል። የሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊዎች እና ተሳታፊ ጋዜጠኞች ዛሬ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በሴት ጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ ከሆኑት መካከል ዩጋንዳዊቷ ጋዜጠኛ አይባሬ ሲንደሬላ ኢትዮጵያ በዜጎቿ አስተዋጽኦ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት ያሳየችውን ቁርጠኝነት አድንቃለች። በበርካታ ሀገራት ዜጎች ከሚከፍሉት ታክስ ተጨባጭ ውጤቶችን እምብዛም ሲያዩ አይስተዋልም ያለችው ጋዜጠኛዋ ኢትዮጵያ በግልጽነትና በጠንካራ ራዕይ የህዝብን ሀብቶች አሻጋሪ ብሄራዊ ፕሮጀክት መቀየሯን ተናግራለች። የአፍሪካ መሪዎች ከሕዳሴ ግድብ ጠቃሚ ተሞክሮዎችን ሊወስዱ ይገባል ብላለች። የኬንያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከፍተኛ አዘጋጅ አሻ ሃሚሲ አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግሮች ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት መፍታት እንዳለባቸው ገልጻለች። ሕዳሴ ግድብ ዜጎች ለሀገራቸው መስዋዕትነት እንደሚከፍሉ የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው ያለችው አሻ ይህም በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለ መተማመንና ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ ላይ መስራት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላከት ነው ብላለች። ግድቡ አፍሪካውያን ለጋራ ራዕይ ከቆሙ ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነም ተናግራለች። በኢጋድ ሚዲያ ሽልማት በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ ካሸነፉት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው ደቡብ ሱዳናዊው የፊልም ባለሙያ እና ተራኪ ጋብርኤል ጋትሉዋክ ዋል ኬት በበኩሉ ህዳሴ ግድብ አፍሪካ ያላትን አቅም በተግባር ያሳየ ነው ሲል ተናግሯል። ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የመሰለ ግዙፍ ፕሮጀክት ካሳካች ሌሎች ሀገራትም ይህን ፈለግ ተከትለው ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ ይችላሉ ብሏል። አፍሪካውያን ሀገራቸውን በራሳቸው መገንባት እንደሚችሉ ማመን አለባቸው ያለው ኬት የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ሌሎች እንዲወስኑላቸው መፍቀድ የለባቸውም ሲልም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ለሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን እና በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት አንስተዋል። ሕዳሴ ግድ የአፍሪካ የስኬት ተምሳሌት ፕሮጀክት እንደሆነ ገልጸው ከግድቡ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ጎረቤት ሀገራትን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አመልክተዋል። ይህም ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ራዕይ የሆነውን የበለጸገች እና የተሳሰረች አፍሪካን የመፍጠር ራዕይን እንደሚደግፍም ተናግረዋል። ግድቡ የአፍሪካን ትርክት የመቀየር ትልቅ ኃይል ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል አምባሳደሩ።
የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል
Nov 21, 2025 738
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ገለጸ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዘጋጅነት የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችና የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ላይ የዌብናር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ የገንዘብ ተቋማት፣ ተመራማሪዎችና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የልማት ዕቅድ ክፍል ኃላፊ ኦዬባንኬ አበጂሪን፤ የምንፈልጋትን አፍሪካ ዕውን ለማድረግ በዘላቂ የልማት ግቦች ላይ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት የ2030 ዘላቂ የልማት አጀንዳና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 አፈፃጸም ሂደትን የሚከታተል የሪፖርት ሥርዓት መኖሩንም ገልጸዋል። እ.ኤ.አ በ2017 የተጀመረው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት ክትትል ሥርዓትም የአህጉሪቷን ዘላቂና ቁልፍ የልማት ማዕቀፎች አፈፃጸም የሚገመገምበትን መድረክ በማመቻቸት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርት መድረክም የአህጉሪቷ ልማት በሳይንስና ማስረጃ የተመሰረቱ የመፍትሔ አፈፃጸሞችን ያመላከተ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሪፖርቱም የአፍሪካ ዕድገት በጤና፣ በሥርዓተ ፆታ እኩልነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በውቅያኖስ ጥበቃና ዓለም አቀፍ ሽርክና ጋር በአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ የ2030 ዘላቂ የልማት ግብና የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 ወሳኝ አካል መሆኑን አስረድተዋል። የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካትም በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ የትብብር ሥርዓትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የ2025 የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ሪፖርትም ወሳኝ የአፈፃጸም ግኝቶችን በማረም የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን በሚገባ ለመተግበር አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። በመድረኩም የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት ግቦችና አጀንዳዎች የአፈፃጸም ስኬት ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመቅረጽ የሚችል ተግባቦት መፈጠሩን አስገንዝበዋል። በቀጣይም የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካትም አዲስ ዓለም የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ አስፈላጊነትን ታሳቢ በማድረግ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። መድረኩም ብሔራዊና ቀጣናዊ የልማት ስኬት አፈፃጸም የአሰራር ስርዓቶችን በመፈተሽ ዕድሎችን በማስፋት የአህጉሪቷን ዘላቂ የልማት አጀንዳዎ ማሳካት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነት አድማሳቸውን ለማስፋት እንደሚሰሩ ገለጹ
Nov 20, 2025 626
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ በትምህርት እና ዲጂታል ዘርፍ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በአፍሪካ ህብረት ዋና ኮሚሽን ዛሬ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረቱን የጎበኙ የመጀመሪያ ማሌዥያ መሪ ሆነዋል።   የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ መስኮች ያላቸውን አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው። ሊቀመንበሩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአፍሪካ እና ማሌዥያ ትብበር ውስጥ ታሪካዊና የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር እንደሚያጠናክር አመልክተዋል። እ.አ.አ በ2024 የአፍሪካ እና ማሌዥያ የንግድ ልውወጥ መጠን 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቅሰው፤ ይህም በዘርፉ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ትምህርት የሁለቱ ወገኖች አጋርነት ዋነኛ ምሰሶ መሆኑንና ከእ.አ.አ 2012 አንስቶ ከ40 ሺህ በላይ አፍሪካውያን በማሌዥያ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን ገልጸዋል።   ማሌዥያ ቀጣይ የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ሊቀ መንበር መሆኗ እና ብሪክስን ለመቀላቀል ያላት ፍላጎት ኢንቨስትመንትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው ያሉት። ሁለቱ ወገኖች በዲጂታል ኢኖቬሽን፣ በግብርና ማቀነባበሪያ ልማት፣ በደቡብ ደቡብ ንግድ እና ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ ዓመታዊ ምክክር እ.አ.አ በ2026 እንዲካሄድ ሀሳብ አቅርበዋል። የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በበኩላቸው፤ ማሌዥያ እና አፍሪካ ንግድ፣ ግብርና እና ትምህርትን ጨምሮ በቁልፍ ጉዳዮች ትብብር እያደገ መምጣታቸውን አመልክተዋል።   ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ በማስፋት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው መግለጻቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በውይይቱ ላይ የማሌዥያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ህብረት እና ማሌዥያ የአጋርነታቸውን አድማስ ለማስፋት እንደሚሰሩ ገልጸዋል::
ሐተታዎች
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 591
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል።   የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው።   ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።  
 የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 778
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 808
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው።   በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው።   የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው።   “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።   አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።   በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል።   በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 853
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ 
Dec 8, 2025 224
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።  
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2857
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2798
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3696
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 2134
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1386
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7203
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5695
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57965
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52703
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33383
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30907
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 26750
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 25498
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 25070
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 25050
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 57965
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 52703
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 33383
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 30907
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 572
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው።   እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም።   የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል።   የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል።   ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!
ብልህ ከችግር ይማራል!!
Dec 2, 2025 375
ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል!! በማሙሽ ጋረደው ገራድ ተስፋዬ ተፈራ ትውልድና እድገታቸው በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ቃልሻ ቀበሌ ሲሆን በ1999 ዓ.ም በህገ ወጥ መንገድ ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው እንደነበር ያስታውሳሉ። ገንዘብ ለማግኘትና የመለውጥ ህልማቸውን ለማሳካት በሚል ሩቅ አስበው የጀመሩት ህገ ወጥ ጉዞ መዳረሻውን እስር ቤት አደረገው። ይህም ሁኔታ ''ሩቅ አሳቢ-ቅርብ አዳሪ'' አደረጋቸው። በባዕድ አገር በነበራቸው የ2 ዓመት የእስር ቤት ቆይታም የምግብ እጦትን ጨምሮ አካላዊ ጥቃትና ጉልበት ብዝበዛ እንዲሁም የተለያዩ ስነ-ልቦናዊ ጉዳቶችን እንዳስተናገዱ ይናገራሉ።   ይህም አልበቃ ብሎ ከአካባቢው በህገወጥ መንገድ የሚሰደዱ ወጣቶችን ጉልበት በመጠቀም ሰፋፊ እርሻዎች ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ የጉልበት ብዝበዛ ይፈፀምባቸው እንደነበርም ያስታውሳሉ። ብልህ ከደረሰበት ችግር ይማራል! የሚሉት ገራድ ተስፋዬ ሩቅ ሳይጓዙ፣ ገንዘብ ሳያወጡ ሰርተው መለወጥ የሚችሉበትን አካባቢያቸውን ፀጋ ሳያማትሩ ስደት መሄዳቸው ቁጭት ፈጥሮባቸው ነበር፡፡ ይህም በሀገራቸው እንኳንስ የለማን መሬት ይቅርና የተቦረቦረ መሬትን አልምቶ ጉልበትንና ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ለስኬት መብቃት እንደሚቻል ከእስር ቤት ቆይታቸው ተምረው ከእስር እንደተፈቱም ወዲያውኑ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን ተናግረዋል። በ2001 ዓ.ም ወደ ሀገር ቤት እንደተመለሱም በማህበር ተደራጅተው ከመንግሥት ባገኙት 70 ሺህ ብር ብድር በእንስሳት እርባታ ላይ ለመሰማራት 4 የወተት ከብቶችን ገዝተው የእርባታ ስራ መጀመራቸውን ይገልጻሉ፡፡   በዚህም የዞኑ አስተዳደር የሰጣቸውን መሬት አልምተው የእንስሳት እርባታውን አስፋፍተው መስራት ጀመሩ፡፡ አሁን ላይ የወተት ላሞቹን ቁጥር 37 በማድረስ የወተት ምርታማነታቸው አድጎ ከቤት ፍጆታ አልፎ ለሆሳዕና ከተማና አካባቢው በቀን ከ670 ሊትር በላይ ወተት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ለ40 ወጣቶችም ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ከመፍጠራቸውም ባሻገር የተለያዩ የጭነትና የስራ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራት መቻላቸውን ይናገራሉ። የጀመሩትን ስራ በጥምር ግብርና የማስፋትና የሚያገኙትን ወተት በማቀነባበር ምርቱን በተለያየ መልኩ ለገበያ የማቅረብ ራዕይን ሰንቀው በትጋት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በህገወጥ ስደት ካጋጠማቸው ችግር ተነስተው በተግባር ያዩትን ለሌሎች በማስተማር የስደትን አስከፊነት ለአካባቢያቸው ወጣቶች እያስገነዘቡ መሆኑን ገልጸዋል።   ወጣቶች የስደትን አማራጭ ከመመልከታቸው በፊት የአካባቢያቸውን ፀጋ እንዲቃኙና ራዕይ ሰንቀው ራሳቸውን ለማሻሻል እንዲሰሩም መክረዋል። መለወጥ በውጪ ሀገር ብቻ ያለ የሚመስላቸው የቤተሰብ ኃላፊዎችም ልጆቻቸው በሀገራቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ በማመን ሊያግዟቸው እንደሚገባም አቶ ገራድ አስገንዝበዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወልደስላሴ፤ በክልሉ በርካታ ወጣቶች ያልተጨበጠ ተስፋ ሰንቀው ለህገወጥ ስደትና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡   በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ የሚያስችል አቅም በግብርናው ዘርፍ መኖሩን ጠቅሰው በዘርፉ የተሰማሩ ከስደት ተመላሾች በአካባቢያቸው ሰርተው ለስኬት እየበቁ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ ስራ አጥ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ላይ የሚገኙና የእነዚህን አካላት ተሞክሮ በመውሰድ በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ መትጋት ይገባል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም