ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በተጠባቂው ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ እና ቼልሲ አቻ ተለያዩ
Jan 4, 2026 87
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ20ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንችስተር ሲቲ እና ቼልሲ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቋል። ማምሻውን በኢትሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቲጃኒ ራይንደርስ በ42ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ማንችስተር ሲቲን መሪ አድርጓል። ኢንዞ ፈርናንዴዝ በ94ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ባሳረፈው ግብ ቼልሲ አቻ ወጥቷል። ባለሜዳው ማንችስተር ሲቲ በኳስ ቁጥጥር እና ኢላማ የጠበቁ ሙከራዎችን በማድረግ የተሻለ ነበር። ውጤቱን ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ በ42 ነጥብ ደረጃውን ከሶስተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ወደ ስድስት ከፍ ብሏል። ቼልሲ በ31 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ዛሬ በተደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ሊድስ ዩናይትድ አንድ አቻ ሲለያይ፣ የፉልሃም እና ሊቨርፑል ጨዋታ ሁለት አቻ ተጠናቋል። ብሬንትፎርድ ኤቨርተንን 4 ለ 2፣ ኒውካስትል ዩናይትድ ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 0 አሸንፈዋል። ቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ሰንደርላንድ አንድ አቻ ተለያይተዋል። የዛሬ ጨዋታዎችን ተከትሎ የ20ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የ21ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳሉ።
ምሁራን ጠያቂ፣ አሰላሳይና በፈተና ውስጥ አልፎ ሀገር የሚገነባ ትውልድ የማፍራት ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jan 4, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ ምሁራን ጠያቂ፣ አሰላሳይና ሀገር ወዳድ ትውልድ የመፍጠር እንዲሁም በፈተና ውስጥ አልፎ ሀገር የሚገነባ ትውልድ የማፍራት ኃላፊነት እንዳለባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሁፍ አቅርበዋል። በዚህም የምሁርነትን ምንነት፣ መገለጫና ተግባራዊ ሚናን አስመልክቶ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪቸውም ምሁራን ከሌላው ማኅበረሰብ የሚለዩት ባላቸው እሳቤና ተግባር መሆኑን ጠቅሰው ምሁርነት ለጥያቄ ዝግጁ መሆንና የመጠየቅ ብቃት ነው ብለዋል፡፡ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሄድ ለምሁርነት አንድ ደረጃ ወደ ፊት የሚያስኬድ ቢሆንም እውነተኛ ምሁርነት ግን በጥያቄ ውስጥና ከጥያቄ በኋላ በሚገኝ የመጠየቅ ብቃትና ትጋት የሚለካ መሆኑን ገልጸዋል። ምሁርነት ውስብስብ ጉዳዮችን ለመዳሰስ መሞከር፣ ሐሳብን ለመናገር፣ ለማድመጥና ለመጠየቅ መዘጋጀት መሆኑን ጠቅሰው ይህም በዋናነት በማሰብ አቅም ግንባታ ላይ የሚሠራ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። ከማሰብ አቅም ባለፈ ብልህነት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመውም ብልህነት ስሜታዊ ብልህነትን፣ ማኅበራዊ ብልህነትንና የማሰብ አቅምን የሚያቅፍ መሆኑን አብራርተዋል። ሀገሪቱ ዘመን ቀያሪና ትውልድ አሻጋሪ እሳቤዎች እንደሚያስፈልጓት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሁራን መገለጫ ሐሳብ አክባሪና አፍቃሪ፣ ጥልቅ አሰላሳይና ብዙ ጠያቂ፣ አንባቢና ነቃሽ ተንታኝ፣ እንዲሁም ችግር ፈቺና መፍትሔ አሳሽ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል። ምሁራን ነገሮችን ከተለመደው መንገድ በተለየ መልኩ የማየት፣ ውስብስብ ጉዳዮችን የመተንተንና ዕውቀትን ወደ ሚጨበጥ ተግባር የመቀየር ብቃት ሊኖራቸው እንደሚገባም አክለዋል። ምሁራን ትውልዳዊ፣ ማኅበረሰባዊ፣ ኢንዱስትሪያላዊና ዓለም አቀፋዊ ሚናዎች እንዳሏቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጠቁመዋል። ምሁራን ጠያቂ፣ አሰላሳይና ሀገር ወዳድ ትውልድ የመፍጠር እንዲሁም በፈተና ውስጥ አልፎ ሀገር የሚገነባ ትውልድ የማፍራት ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ማኅበረሰቡን ከማንቃት ባለፈ፣ በምርምር የተገኙና በሰነድ ተቀምጠው የቆዩ የፈጠራ ንድፎችን ወደ ተግባር መቀየር እንደሚገባቸውም ነው የተናገሩት። የምሁራንን ተግባራዊ ሚና በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚመደቡ ጠቁመው የዕውቀት ዘር መዝራት፣ የለውጥ አቅጣጫ መቀየስ እና የወል እሴትን መበየን መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ምሁር ከቀደምቶችና ከታሪክ የተገኘውን ዕውቀት ለዘመኑ በሚመጥን መልኩ ቅርጽ ማስያዝ፣ መከራከርና ዕውቀቱ ዓለም አቀፋዊ እንዲሆን ማድረግ ይገባዋልም ነው ያሉት። የፈጠራ፣ የሥራ፣ የዴሞክራሲ፣ የሲቪክና የጽዱ ከተማ ባህልን የሚያጎለብቱ ሐሳቦችንና እሴቶችን መፍጠር እንዲሁም ለውጥን መተግበር የሚያስችሉ የጋራ እሴቶችን መቅረጽ አለባቸው ብለዋል፡፡ ምሁራን ሥርዓታዊ፣ ስልታዊ፣ ፈጠራዊና አመክንዮአዊ እሳቤዎች ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባቸው አስገንዝበው ምሁራን ለሁሉም እሳቤዎች አስኳል መሆናቸውን ተናግረዋል።
ምሁራን የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የጋራ ትርክትን በመፍጠር ምሁራዊ አመራር መሥጠት አለባቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jan 4, 2026 96
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ ምሁራን ከድህነት የተላቀቀችና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የጋራ ትርክትን በመፍጠር ምሁራዊ አመራር መሥጠት እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሁፍ አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጽሁፋቸው፤ ከሀገር ብልጽግና ከፍተኛ ሚና ያለው ምሁር በዘርፉ የተሰጠውን አመራር ለይቶና አውቆ የሚያገለግል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምሁራን ከድህነት የተላቀቀችና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የጋራ ትርክትን በመፍጠር ምሁራዊ አመራር መሥጠት አለባቸው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያን ከድህነት አዙሪት አውጥቶ ወደ ተሟላ ብልጽግና ለማሸጋገር ምሁራን ሚናቸው የጎላ መሆኑን በማንሳት፤ ውጤታማ አመራር ለመስጠት በቅድሚያ ራስን ማሸነፍ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ መሪነት የሚጀምረው ከራስ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ምሁራን በውስጣቸው ያለውን ድምጽ ለይተው ማድመጥና ድል መቀዳጀት አለባቸው ብለዋል፡፡ ምሁራን የተሰጣቸውን ኃላፊነት፣ ዕውቀትና ተጽዕኖ ተጠቅመው ውጤታማ አመራር ለመስጠት ወሳኝ ሚና እንዳላቸውም አንስተዋል፡፡ መሪነት በጊዜና በዘመን ላይ መሰልጠን መሆኑን ገልጸው፤ እያንዳንዱን ቅጽበት ለታለመለት ዓላማ ማዋል ይገባል ነው ያሉት፡፡ የምሁርነት መገለጫ ከጊዜ ጋር የሚደረግን እሽቅድምድም ሳይቀደሙና ሳያረፍዱ መገኘት መሆኑን በመጥቀስ፤ ያሉበትን ዘመን የሚረዱ ውጭውን ማየት የሚችሉ መሆን እንዳለባቸውም ገልጸዋል፡፡ ሀሳብ የለውጥ ሀይል ምሁራን ደግሞ የለውጥ ወኪል ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በፖለቲካ በኢኮኖሚ እና በሰዎች መስተጋብር የሀሳብ ውክልናቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል፡፡ ሀሳብ እንቅስቃሴ ይፈጥራል፤ እንቅስቃሴ ስርዓት ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የምሁራን ሀሳብ ተቋም መፍጠር አለበት ብለዋል፡፡
የገዳ ስርአት እሴቶችን በማስረጽ በህዝቡ ውስጥ ሰላምና አብሮነት እንዲጎለብት እየተሰራ ነው
Jan 4, 2026 73
መተሓራ ፤ታህሳስ 26/2018 (ኢዜአ):- የገዳ ስርአት እሴቶችን በማስረጽ በህዝቡ ውስጥ ሰላምና አብሮነት እንዲጎለብት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ። ትውልዱ የገዳ ስርአት እሴቶችን በመጠበቅ ለአብሮነት እና አንድነት መጽናት የበኩሉን መወጣት እንዳለበት ተመላክቷል። የከረዩ ሚችሌ ገዳ ስልጣኑን ወደ ሀልችሳ የጎባ የሚያስረክብበት የስልጣን ርክክብ ስርዓት ‘ቡታ ቀሉ’ መርሃ ግብር በምስራቅ ሸዋ ዞን መተሃራ አካባቢ ተሬ ሌዲ በተባለ ስፍራ እየተካሄደ ይገኛል። የሚችሌ አባ ገዳ ቡላ ዲዶ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት በጥንታዊ የገዳ ስርዓት መሰረት ህዝቡ በሰላም አብሮ እንዲኖር ሚናቸውን ሲወጡ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የገዳ ስርዓት እሴቶች ሰላምን ማጽናት እና የህዝቡን አብሮነት የሚያጠናክሩ ለጋራ ልማት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ናቸው ብለዋል። በቀጣይም ትውልዱ ባህሉን በመጠበቅ አብሮነትንና አንድነትን ለማጽናት ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በተለይም ባለፉት ዓመታት የገዳ ስርአት እሴትን በማስተማር በህዝቡ ውስጥ ሰላምና አንድነት እንዲጎለብት መሰራቱን ጠቅሰዋል። ትውልዱ በገዳ ስርዓት እሴት በመታነፅ ከመጤ ባህል ተጽእኖ ራሱን እንዲጠብቅ ለማስቻል እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የቦረና ኦሮሞ ባህልና ታሪክ ተመራማሪ የሆኑት አቶ ገልማ ጎሎ ዳባ በበኩላቸው የገዳ ስርዓት በርካታ ጠቃሚ እሴቶች ያሉት ነው ብለዋል። ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት መሰረት የሆነው የገዳ ስርዓት አብሮነት እና አንድነትን የሚያጸና በመሆኑ በትውልዱ ሊጠበቅ እንደሚገባ አስረድተዋል። የገዳ ስርአት ለትውልድ እንዲተላለፍ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በየስምንት ዓመቱ የሚደረገው የስልጣን ርክክብ የገዳ ስርዓት እሴት እየተሸጋገረ እንዲሄድ እያደረገው መሆኑን ጠቅሰዋል። ሌላው የኦሮሞ ባህልና ታሪክ ተመራማሪና መምህር የሆኑት አስሀፋ ተፈራ ( ዶ/ር) የገዳ ስርዓት ለሰላም እና አብሮነት ጠቃሚ እሴቶች እንዳሉት ጠቅሰዋል። “ስርአቱ በመጤ ባህል እንዳይበረዝ በጥናትና ምርምር የመደገፍ ስራ እየሰራን ነው “ብለዋል። ተተኪው ትውልድ ከመጤ ባህል ተጽእኖ ራሱን በመጠበቅ በገዳ ስርዓት እሴት እንዲታነጽ እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል። የህዝቡን ባህልና ቋንቋ የማልማትና የማሳደግ እንዲሁም የገዳ ስርዓት እሴት ለትውልድ እንዲተላለፍ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክተው እንደሚቀጥሉ አመላክተዋል። የከረዩ ኦሮሞ የገዳ ስልጣን ሽግግር ስነ-ስርዓት ታህሳስ 26 እና 27 ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ በድምቀት እየተካሄደ ይገኛል።
ሲዳማ ቡና ሀድያ ሆሳዕናን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ
Jan 4, 2026 66
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ሲዳማ ቡና ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ መስፍን ታፈሰ እና ዮሴፍ ዮሐንስ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በውድድር ዓመቱ ስምንተኛ ድሉን ያስመዘገበው ሲዳማ ቡና በ28 ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። ከሶስት ተከታታይ ድሎች በኋላ ሽንፈት ያስተናገደው ሀድያ ሆሳዕና በ16 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። በሌሎች ጨዋታዎች ምድረገነት ሽሬ ኢትዮጵያ ቡናን 3 ለ 1 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሽመክት ጉግሳ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ዳንኤል ዳርጌ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። አቡበከር አዳሙ በፍጹም ቅጣት ምት ለኢትዮጵያ ቡና ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ሸገር ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ዳዊት ካሳው በጨዋታ ለሸገር ከተማ በጨዋታ፣ አዲስ ግደይ በፍጹም ቅጣት ምት ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ነጌሌ አርሲ መቻልን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዳዊት ተፈሪ እና አለኝታ ማርቆስ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
ፖለቲካ
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ መሠናክሎች ሳይበግሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል
Jan 4, 2026 150
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበግሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል ሲሉ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ገለጹ። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል ለወራት ያሰለጠናቸውን መሠረታዊ ወታደሮች በዛሬው ዕለት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል። ተመራቂዎቹ የመሠረታዊ ውትድርናን እና የመሠረታዊ ኮማንዶ ምልመላ መስፈርቶችን ያሟሉ ናቸው። በምረቃ መርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ፤ የውትድርና ሙያ የጀግንነት ስብዕና የተላበሰ ማንነትን የሚፈልግ ከመሆኑም በላይ ፈታኝ ለሆኑ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩ በፅናት መቆምን ይጠይቃል ብለዋል። ይህ ሲሆን በሚያልፍ ህይወት የማያልፍ ታሪክን በመፃፍ በዜጎች ልብ ውስጥ በትውልድ ቅብብሎሽ ለዘለዓለም መኖር እንደሚቻልም ጀነራል መኮንኑ ገልፀዋል። የመሠረታዊ ውትድርናን አጠናቀው የተመረቁት ወታደሮች በቀጣይ ከኮማንዶ ከአየር ወለድ ከልዩ ኃይልና ፀረ-ሽብር እንዲሁም ከሪፐብሊኩ የጥበቃ ኃይል ጋር ለመቀላቀል የሚያስችላቸውን ስልጠና በብቃት እንዲወጡም አሳስበዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝና የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል አመራርና አባላት ኢትዮጵያ አስቸጋሪ ሁኔታዎች በገጠሟት ጊዜ ሁሉ አለኝታነታቸውን በተግባር ያረጋገጡ የቁርጥ ቀን ልጆች መሆናቸውንም ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ገልፀዋል። ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ጠንካራ የአካል ብቃት፣ የተኩስና የተለያዩ የውጊያ ስልቶችን በቀንና በሌሊት የተማሩና በልምምድ ያዳበሩ ከመሆኑም በላይ የስነ-ልቦናና የጤና ትምህርትን የቀሰሙ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል አዛዥ ብርጋዲየር ጄነራል ቦጃ አጋ ናቸው። ማሠልጠኛ ማዕከሉ የቅበላ አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደጉን የገለፁት ብርጋዲየር ጄነራል ቦጃ አጋ የሥልጠና መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት ተችሏልም ብለዋል። ተመራቂዎች በስልጠና ቆይታቸው አሠልጣኞችና አመራሮች እነሱን ለማብቃት ላደረጉት ሁለንተናዊ ጥረት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይ ለሚጠብቃቸው የመሠረታዊ ኮማንዶ ስልጠና ዝግጁ መሆናቸውን መግለጻቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያደረሰን ዘገባ ያመለክታል።
ሰላማዊ የፖለቲካ ባሕል ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት መሠረት ነው
Jan 4, 2026 96
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ ሰላማዊ የፖለቲካ ባሕል ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት ወሳኝ መሠረት መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር በመተባበር "ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ለሰላማዊ ምርጫ" በሚል መሪ ሀሳብ የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል። የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ በመድረኩ እንደተናገሩት፤ ምርጫ ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለዴሞክራሲ ሥርዓት መጠናከር ዋነኛው ምሰሶ ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገር ሰላምና ደኅንነት በማስጠበቅ ረገድ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው ጠቁመው፤ ለሰላማዊ ምርጫ ሂደትም ቁልፍ ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል። በተለይ በምርጫ ወቅትም ሆነ በሌሎች ጊዜያት የሚደረጉ ማናቸውም የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች የሀገርን አንድነትና የሕዝብን ደኅንነት በጠበቀ መልኩ መከናወን እንዳለባቸው ተናግረዋል። ሰላማዊ ምርጫን ማረጋገጥ የመንግሥት ብቻ ተግባር ሳይሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራት ድርጅቶችና የመላውን ሕዝብ የተቀናጀ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱ ጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባትና የመድብለ ፓርቲ ሥርዓትን ለማጠናከር የበኩሉን ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን ምክር ቤቱ አስፈላጊውን የዝግጅት ሥራ እያከናወነ መሆኑን አመላክተዋል።
በአማራ ክልል የዘላቂ ሰላምና ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jan 3, 2026 188
ባህር ዳር፤ ታህሳስ 25/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የዘላቂ ሰላምና ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) ገለጹ። የአስተዳደር ክላስተር የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በባህር ዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ሰላምን ከማስፈን ባለፈ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል። የክልሉን ሰላም ለማወክ የተንቀሳቀሱ የጥፋት ቡድኖችን በመከታተል ጠንካራ ህግ የማስከበር ስራ መሰራቱን አንስተው፥ የሰላምን መንገድ ተቀብለው የመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችንም መልሶ በማቋቋም ወደ ልማት ስራ እንዲገቡ ተደርገል ብለዋል። በክልሉ በተለይም በከተሞች የአገልግሎት አሰጣጥን የማዘመን፣የዲጅታል አሰራርን የማስፋትና በሁሉም ዘርፎች የልማት ስራዎች እንዲከናወኑ መደረጉን ገልጸዋል። በመሆኑም በክልሉ የዘላቂ ሰላም ግንባታን የሚያስቀጥሉና የህዝብን ተጠቃሚነት እውን የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ አረጋግጠዋል። በቀጣይም በአስተዳደር ክላስተር ክንውን የተገኙ ስኬቶችን ይበልጥ በማጠናከር ለክልሉ ሰላም፣ ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት በላቀ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር)፤ በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ አስተማማኝ ሰላም በመፍጠር ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። ከህግ ማስከበር ስራው በተጓዳኝ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው የመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችን የመልሶ ማቋቋምና ወደ ልማት የማስገባት ስራም መከናወኑን አንስተዋል። ከአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፍሃድ) ጋር የተደረሰውን የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተከትሎ ከተለያዩ አካባቢዎች ታጣቂዎች ትጥቃቸውን እያስረከቡ በሰላም መግባታቸውንና አሁንም በመግባት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ ብርሃኑ ጎሽም በበኩላቸው፤ በክልሉ የፍትህ ስርዓቱን የማዘመንና ተደራሽነቱን የማስፋት ስራ በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በፍጥነትና በጥራት መዝገቦች ተጣርተው ክስ በመመሰረት ውሳኔ እንዲያገኙ እየተደረገ ሲሆን አሰራርን የሚያሻሽሉ ደንቦችና መመሪያዎችን በማዘጋጀትም ጥቅም ላይ እንዲውሉ ተደርጓል ብለዋል። በመድረኩ በክላስተሩ የተካተቱ የተለያዩ ተቋማት ሃላፊዎች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ የስድስት ወሩን ዕቅድ አፈፃፀም በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎች የሚቀመጡ ይሆናል።
የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ ያምናል
Jan 2, 2026 298
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 24/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ እንደሚያምን እና ለተግባራዊነቱም እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ሀሳብ የለውጥ ኃይል ነው። ምሁራን ደግሞ የለውጥ ወኪሎች ናቸው ብለዋል። ምሁራን በማኀበረሰብ ውስጥ የሚፈጥሩት ለውጥም ሀገርን ወደ ብልጽግና እንደሚወስድ ጠቅሰው በዚህ ረገድም ምሁራን ሀሳብ አክባሪና አፍቃሪ፣ ጥልቅ አሰላሳይ፣ አንባቢ፣ ችግር ፈቺና መፍትሄ አሳሽ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አመልክተዋል። በዛሬው እለት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት ዩኒቨርሲቲው ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሁፍ በማቅረብ መሳተፋቸውን ጠቁመዋል። በመድረኩም የኢትዮጵያ ምሁራን በሁለንተናዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ሚና በሚመለከት ሰፊ ውይይት መደረጉን ተናግረዋል። የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ ያምናል፣ ለተግባራዊነቱም እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት። ተቋማቱም የመማር ማስተማር እንዲሁም የምርምር ስራዎችን ከቴክኖሎጂ ጋር በማናበብ ወደ ፈጠራና ተግባር መለወጥ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበው ይህም የኢትዮጵያን ብልጽግና በተደመረ አቅም ለማፋጠን ሚናው ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ጠንካራ ሃገረ መንግስት ለመገንባት ሀገራዊ ምክክሩ ታሪካዊ እድል ነው
Jan 2, 2026 230
አሶሳ፤ታህሳስ 24/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ጠንካራ ሃገረ መንግስት ለመገንባት ሀገራዊ ምክክሩ ታሪካዊ እድል መሆኑን የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በአዋጅ ተቋቁሞ ስራ ከጀመረ በኋላ ከዝግጅት እስከ ምክክር ምእራፍ እስካሁን በርካታ ተግባራትን ማከናወን ችሏል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጉሙዝ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለሜሳ ኔኖ፥ ሀገራዊ ምክክሩ በምክክር ችግሮችን የመፍታት እድል ይዞ የመጣ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ጠንካራ ሃገረ መንግስት ለመገንባት ታሪካዊ እድል መሆኑንም አክለዋል። በመሆኑም ይህንን ታሪካዊ እድል በስኬት ለመቋጨት ሁላችንም በምክክር ችግሮችን የመፍታት ቁርጠኝነት ማሳየት አለብን ብለዋል። በሀገር ውስጥም ይሁን በውጭ የሚኖሩ ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ በመምከርና ለመፍትሄው በመስራት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ባለቤት ሊሆኑ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በዚህ ሂደት ፓርቲያቸው እስካሁን የነቃ ተሳትፎ ማድረጉን አስታውሰዋል። በቀጣይም ምክክሩ በስኬት እስከሚጠናቀቅ ድረስ የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የጉሙዝ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ለምክክር ኮሚሽኑ የተለያዩ አጀንዳዎችን ማስረከቡን አስታውሰው፥ በጉዳዮች ላይ በመምከር የመፍትሄው አካል ለመሆን መዘጋጀቱን ገልጸዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
“ምሁር ማነው?"
Jan 2, 2026 322
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የምሁራን ሚና ለሀገራዊ ብልጽግና” በሚል ርዕስ የጥናታዊ ጽሁፍ እያቀረቡ ይገኛሉ። የአካዳሚያዊ አመራሮችና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ገለጻው እየተሰጠ ይገኛል። የዛሬው መርሃ ግብር 75ኛ ዓመት በዓሉን ለማክበር ላለፉት ሳምንታት ሲደረጉ የነበሩ ተከታታይ ገለጻዎች እና ፕሮግራሞች ማጠቃለያ ነው። #PMOEthiopia
ሀገራዊ ምክክር ልዩነቶቻችንን በሰለጠነና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያገኘነው የማይተካ ዕድል ነው
Jan 2, 2026 273
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 24/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የተጀመረው ሁሉን አካታች የሆነ ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶቻችንን በሰለጠነና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያገኘነው የማይተካ ዕድል ነው ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ፡፡ አገልግሎቱ፥ ምክክር ለጋራ አሸናፊነት፣ ምክክር ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገረመንግሥት ግንባታ! በሚል ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ለዘመናት ያለመግባባትና የንትርክ እንዲሁም የእርስ በርስ ግጭት ምንጭ የነበረው ኋላቀር የፖለቲካ ባህላችን የወለደው ችግር ነው ብሏል። ይህን ችግር በመሠረታዊነት ለመቅረፍ እና በሀገራዊ ጉዳዮችና በብሔራዊ አጀንዳዎች ዙርያ የሚታዩ ልዩነቶችንና መካረሮችን ለማረቅ ሀገራዊ ምክክር ወሳኝ ጉዳይ ነው ሲል ነው የገለጸው፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፦ መንግሥት አዎንታዊ የሰላም ባህል እንዲሰፍንና የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል ተገንብቶ ኢትዮጵያውያን ችግሮቻቸውን በጠረጴዛ ዙርያ በሃሳብ አውድ ብቻ መፍታት አለባቸው የሚል ፅኑ እምነት አለው፡፡ለዚህም ተግባራዊነት በቁርጠኝነት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ የተጀመረው ሁሉን አካታች የሆነ ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶቻችንን በሰለጠነና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያገኘነው የማይተካ ዕድል ነው፡፡ ይህ ዕድል ለሁሉም አካላት የተከፈተ የትኛውንም ወገን የማይለይ አካታች የምክክር ዕድል ነው፡፡ በዚህ እድል ለመጠቀም ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ዝግጁ ልንሆን ይገባል፡፡ ይህ ዕድል የኖረውን የወንድማማችነት ዕሴት ያዳከመውን የተበላሸ የፖለቲካ ባህላችንን ከማከም ባለፈ ዘላቂ ሰላማችንን ለማረጋገጥ ቁልፍ ጉዳይ ነው። የምክክር ዕድሉ በመሰረታዊ ጉዳዮቻችን ዙርያ ሃገራዊ መግባባት ለመፍጠር ፣እየዳበረ የሚሄድ የዲሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ብሎም በመሃከላችን የእርስ በእርስ መተማመንን በመፍጠር የህዝቦችን መተባበር እና አንድነት በማረጋገጥ የማይተካ ሚና ይኖረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ ጦርነትና አብዮት የተሟላ መፍትሔ የማያመጡ መሆናቸውን በተግባር የተረጋገጠ ጉዳይ ነው፡፡ በሁለቱም መንገድ የመጣ አሸናፊነት ጊዜያዊና መልሶ ቁርሾና ቂምን የሚያሳድር መንገድ መሆኑን ተምረንበታል፡፡ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት በውይይትና በምክክር ችግሮቻቸውን አለመግባባቶቻቸውን የመፍታት ድንቅ ባህል የነበራቸው ህዝቦች ናቸው፡፡ ነገር ግን ይህ እሴት እየጎለበተ በመጣው ኋላቀር የፖለቲካ ባህል ምክንያት ከጊዜ ወደጊዜ በመደብዘዝ ከፋፋይ ነጠላ ትርክት መገለጫችን እስከመሆን ደርሷል፡፡ በአለም ላይ በርካታ ሀገራት ከከረረ ልዩነትና ከግጭት ድባብ ለመውጣት ሀገራዊ ምክክር እንደመፍትሄ ተጠቅመዋል፡፡ እኛም ኢትዮጵያውያን ይህንን ማድረግ የማይሳነን ሕዝቦች ለመሆናችን በየአካባቢው ያሉ ባህላዊ ዕሴቶቻችን ማሳያ ናቸው፡፡ ስለሆነም ዘላቂ የሆነ መፍትሔን ለማምጣት በእውነተኛ ፖለቲካዊ መሻት በቅንነት ለውይይት ለሰጥቶ መቀበልና ለጋራ መፍትሔ ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት መነሳት ይኖርበታል፡፡ ኢትዮጵያውያን የመጣንበት የግጭትና የጦርነት አዙሪት በቃን የምንልበት ትክክለኛው ሰዓት አሁን ነው፡፡ ግጭት ማንንም አሸናፊ የማያደርግ የጥፋት አዙሪት ስለሆነ የሀገራዊ ምክክር ሂደትን ስኬታማ ማድረግ ፣ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ የህግ የበላይነትን ማስፈን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የምትሆን ሀገር ለመገንባትና ሁላችንንም የጋራ አሸናፊ ለማድረግ ያግዘናል፡፡ በመሆኑም ሁሉም አካል በምክክሩ በንቃት እንዲሳተፍ በዚህ አጋጣሚ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡ ምክክር ለጋራ አሸናፊነት፣ ምክክር ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገረመንግሥት ግንባታ! የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ታኅሣሥ 24/2018 ዓ.ም
ፖለቲካ
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ መሠናክሎች ሳይበግሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል
Jan 4, 2026 150
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበግሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል ሲሉ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ገለጹ። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል ለወራት ያሰለጠናቸውን መሠረታዊ ወታደሮች በዛሬው ዕለት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል። ተመራቂዎቹ የመሠረታዊ ውትድርናን እና የመሠረታዊ ኮማንዶ ምልመላ መስፈርቶችን ያሟሉ ናቸው። በምረቃ መርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ፤ የውትድርና ሙያ የጀግንነት ስብዕና የተላበሰ ማንነትን የሚፈልግ ከመሆኑም በላይ ፈታኝ ለሆኑ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩ በፅናት መቆምን ይጠይቃል ብለዋል። ይህ ሲሆን በሚያልፍ ህይወት የማያልፍ ታሪክን በመፃፍ በዜጎች ልብ ውስጥ በትውልድ ቅብብሎሽ ለዘለዓለም መኖር እንደሚቻልም ጀነራል መኮንኑ ገልፀዋል። የመሠረታዊ ውትድርናን አጠናቀው የተመረቁት ወታደሮች በቀጣይ ከኮማንዶ ከአየር ወለድ ከልዩ ኃይልና ፀረ-ሽብር እንዲሁም ከሪፐብሊኩ የጥበቃ ኃይል ጋር ለመቀላቀል የሚያስችላቸውን ስልጠና በብቃት እንዲወጡም አሳስበዋል። የልዩ ዘመቻዎች ዕዝና የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል አመራርና አባላት ኢትዮጵያ አስቸጋሪ ሁኔታዎች በገጠሟት ጊዜ ሁሉ አለኝታነታቸውን በተግባር ያረጋገጡ የቁርጥ ቀን ልጆች መሆናቸውንም ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ገልፀዋል። ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ጠንካራ የአካል ብቃት፣ የተኩስና የተለያዩ የውጊያ ስልቶችን በቀንና በሌሊት የተማሩና በልምምድ ያዳበሩ ከመሆኑም በላይ የስነ-ልቦናና የጤና ትምህርትን የቀሰሙ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል አዛዥ ብርጋዲየር ጄነራል ቦጃ አጋ ናቸው። ማሠልጠኛ ማዕከሉ የቅበላ አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደጉን የገለፁት ብርጋዲየር ጄነራል ቦጃ አጋ የሥልጠና መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት ተችሏልም ብለዋል። ተመራቂዎች በስልጠና ቆይታቸው አሠልጣኞችና አመራሮች እነሱን ለማብቃት ላደረጉት ሁለንተናዊ ጥረት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይ ለሚጠብቃቸው የመሠረታዊ ኮማንዶ ስልጠና ዝግጁ መሆናቸውን መግለጻቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ያደረሰን ዘገባ ያመለክታል።
ሰላማዊ የፖለቲካ ባሕል ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት መሠረት ነው
Jan 4, 2026 96
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ ሰላማዊ የፖለቲካ ባሕል ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት ወሳኝ መሠረት መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ ገለጹ። የሰላም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር በመተባበር "ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ለሰላማዊ ምርጫ" በሚል መሪ ሀሳብ የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል። የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ በመድረኩ እንደተናገሩት፤ ምርጫ ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለዴሞክራሲ ሥርዓት መጠናከር ዋነኛው ምሰሶ ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገር ሰላምና ደኅንነት በማስጠበቅ ረገድ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው ጠቁመው፤ ለሰላማዊ ምርጫ ሂደትም ቁልፍ ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል። በተለይ በምርጫ ወቅትም ሆነ በሌሎች ጊዜያት የሚደረጉ ማናቸውም የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች የሀገርን አንድነትና የሕዝብን ደኅንነት በጠበቀ መልኩ መከናወን እንዳለባቸው ተናግረዋል። ሰላማዊ ምርጫን ማረጋገጥ የመንግሥት ብቻ ተግባር ሳይሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራት ድርጅቶችና የመላውን ሕዝብ የተቀናጀ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑንም ገልጸዋል። በመሆኑም ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱ ጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባትና የመድብለ ፓርቲ ሥርዓትን ለማጠናከር የበኩሉን ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል። ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን ምክር ቤቱ አስፈላጊውን የዝግጅት ሥራ እያከናወነ መሆኑን አመላክተዋል።
በአማራ ክልል የዘላቂ ሰላምና ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jan 3, 2026 188
ባህር ዳር፤ ታህሳስ 25/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የዘላቂ ሰላምና ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) ገለጹ። የአስተዳደር ክላስተር የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በባህር ዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ሰላምን ከማስፈን ባለፈ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል። የክልሉን ሰላም ለማወክ የተንቀሳቀሱ የጥፋት ቡድኖችን በመከታተል ጠንካራ ህግ የማስከበር ስራ መሰራቱን አንስተው፥ የሰላምን መንገድ ተቀብለው የመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችንም መልሶ በማቋቋም ወደ ልማት ስራ እንዲገቡ ተደርገል ብለዋል። በክልሉ በተለይም በከተሞች የአገልግሎት አሰጣጥን የማዘመን፣የዲጅታል አሰራርን የማስፋትና በሁሉም ዘርፎች የልማት ስራዎች እንዲከናወኑ መደረጉን ገልጸዋል። በመሆኑም በክልሉ የዘላቂ ሰላም ግንባታን የሚያስቀጥሉና የህዝብን ተጠቃሚነት እውን የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ አረጋግጠዋል። በቀጣይም በአስተዳደር ክላስተር ክንውን የተገኙ ስኬቶችን ይበልጥ በማጠናከር ለክልሉ ሰላም፣ ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት በላቀ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር)፤ በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ አስተማማኝ ሰላም በመፍጠር ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። ከህግ ማስከበር ስራው በተጓዳኝ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው የመጡ የቀድሞ ታጣቂዎችን የመልሶ ማቋቋምና ወደ ልማት የማስገባት ስራም መከናወኑን አንስተዋል። ከአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፍሃድ) ጋር የተደረሰውን የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተከትሎ ከተለያዩ አካባቢዎች ታጣቂዎች ትጥቃቸውን እያስረከቡ በሰላም መግባታቸውንና አሁንም በመግባት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ ብርሃኑ ጎሽም በበኩላቸው፤ በክልሉ የፍትህ ስርዓቱን የማዘመንና ተደራሽነቱን የማስፋት ስራ በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በፍጥነትና በጥራት መዝገቦች ተጣርተው ክስ በመመሰረት ውሳኔ እንዲያገኙ እየተደረገ ሲሆን አሰራርን የሚያሻሽሉ ደንቦችና መመሪያዎችን በማዘጋጀትም ጥቅም ላይ እንዲውሉ ተደርጓል ብለዋል። በመድረኩ በክላስተሩ የተካተቱ የተለያዩ ተቋማት ሃላፊዎች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ የስድስት ወሩን ዕቅድ አፈፃፀም በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎች የሚቀመጡ ይሆናል።
የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ ያምናል
Jan 2, 2026 298
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 24/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ እንደሚያምን እና ለተግባራዊነቱም እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ሀሳብ የለውጥ ኃይል ነው። ምሁራን ደግሞ የለውጥ ወኪሎች ናቸው ብለዋል። ምሁራን በማኀበረሰብ ውስጥ የሚፈጥሩት ለውጥም ሀገርን ወደ ብልጽግና እንደሚወስድ ጠቅሰው በዚህ ረገድም ምሁራን ሀሳብ አክባሪና አፍቃሪ፣ ጥልቅ አሰላሳይ፣ አንባቢ፣ ችግር ፈቺና መፍትሄ አሳሽ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አመልክተዋል። በዛሬው እለት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት ዩኒቨርሲቲው ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሁፍ በማቅረብ መሳተፋቸውን ጠቁመዋል። በመድረኩም የኢትዮጵያ ምሁራን በሁለንተናዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ሚና በሚመለከት ሰፊ ውይይት መደረጉን ተናግረዋል። የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ ያምናል፣ ለተግባራዊነቱም እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት። ተቋማቱም የመማር ማስተማር እንዲሁም የምርምር ስራዎችን ከቴክኖሎጂ ጋር በማናበብ ወደ ፈጠራና ተግባር መለወጥ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበው ይህም የኢትዮጵያን ብልጽግና በተደመረ አቅም ለማፋጠን ሚናው ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ጠንካራ ሃገረ መንግስት ለመገንባት ሀገራዊ ምክክሩ ታሪካዊ እድል ነው
Jan 2, 2026 230
አሶሳ፤ታህሳስ 24/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ጠንካራ ሃገረ መንግስት ለመገንባት ሀገራዊ ምክክሩ ታሪካዊ እድል መሆኑን የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ገለጸ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በአዋጅ ተቋቁሞ ስራ ከጀመረ በኋላ ከዝግጅት እስከ ምክክር ምእራፍ እስካሁን በርካታ ተግባራትን ማከናወን ችሏል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጉሙዝ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለሜሳ ኔኖ፥ ሀገራዊ ምክክሩ በምክክር ችግሮችን የመፍታት እድል ይዞ የመጣ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገራዊ ምክክሩ ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ጠንካራ ሃገረ መንግስት ለመገንባት ታሪካዊ እድል መሆኑንም አክለዋል። በመሆኑም ይህንን ታሪካዊ እድል በስኬት ለመቋጨት ሁላችንም በምክክር ችግሮችን የመፍታት ቁርጠኝነት ማሳየት አለብን ብለዋል። በሀገር ውስጥም ይሁን በውጭ የሚኖሩ ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ በመምከርና ለመፍትሄው በመስራት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ባለቤት ሊሆኑ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በዚህ ሂደት ፓርቲያቸው እስካሁን የነቃ ተሳትፎ ማድረጉን አስታውሰዋል። በቀጣይም ምክክሩ በስኬት እስከሚጠናቀቅ ድረስ የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የጉሙዝ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ለምክክር ኮሚሽኑ የተለያዩ አጀንዳዎችን ማስረከቡን አስታውሰው፥ በጉዳዮች ላይ በመምከር የመፍትሄው አካል ለመሆን መዘጋጀቱን ገልጸዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
“ምሁር ማነው?"
Jan 2, 2026 322
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የምሁራን ሚና ለሀገራዊ ብልጽግና” በሚል ርዕስ የጥናታዊ ጽሁፍ እያቀረቡ ይገኛሉ። የአካዳሚያዊ አመራሮችና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ገለጻው እየተሰጠ ይገኛል። የዛሬው መርሃ ግብር 75ኛ ዓመት በዓሉን ለማክበር ላለፉት ሳምንታት ሲደረጉ የነበሩ ተከታታይ ገለጻዎች እና ፕሮግራሞች ማጠቃለያ ነው። #PMOEthiopia
ሀገራዊ ምክክር ልዩነቶቻችንን በሰለጠነና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያገኘነው የማይተካ ዕድል ነው
Jan 2, 2026 273
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 24/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የተጀመረው ሁሉን አካታች የሆነ ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶቻችንን በሰለጠነና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያገኘነው የማይተካ ዕድል ነው ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ፡፡ አገልግሎቱ፥ ምክክር ለጋራ አሸናፊነት፣ ምክክር ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገረመንግሥት ግንባታ! በሚል ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ለዘመናት ያለመግባባትና የንትርክ እንዲሁም የእርስ በርስ ግጭት ምንጭ የነበረው ኋላቀር የፖለቲካ ባህላችን የወለደው ችግር ነው ብሏል። ይህን ችግር በመሠረታዊነት ለመቅረፍ እና በሀገራዊ ጉዳዮችና በብሔራዊ አጀንዳዎች ዙርያ የሚታዩ ልዩነቶችንና መካረሮችን ለማረቅ ሀገራዊ ምክክር ወሳኝ ጉዳይ ነው ሲል ነው የገለጸው፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፦ መንግሥት አዎንታዊ የሰላም ባህል እንዲሰፍንና የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል ተገንብቶ ኢትዮጵያውያን ችግሮቻቸውን በጠረጴዛ ዙርያ በሃሳብ አውድ ብቻ መፍታት አለባቸው የሚል ፅኑ እምነት አለው፡፡ለዚህም ተግባራዊነት በቁርጠኝነት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ የተጀመረው ሁሉን አካታች የሆነ ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶቻችንን በሰለጠነና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያገኘነው የማይተካ ዕድል ነው፡፡ ይህ ዕድል ለሁሉም አካላት የተከፈተ የትኛውንም ወገን የማይለይ አካታች የምክክር ዕድል ነው፡፡ በዚህ እድል ለመጠቀም ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ዝግጁ ልንሆን ይገባል፡፡ ይህ ዕድል የኖረውን የወንድማማችነት ዕሴት ያዳከመውን የተበላሸ የፖለቲካ ባህላችንን ከማከም ባለፈ ዘላቂ ሰላማችንን ለማረጋገጥ ቁልፍ ጉዳይ ነው። የምክክር ዕድሉ በመሰረታዊ ጉዳዮቻችን ዙርያ ሃገራዊ መግባባት ለመፍጠር ፣እየዳበረ የሚሄድ የዲሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ብሎም በመሃከላችን የእርስ በእርስ መተማመንን በመፍጠር የህዝቦችን መተባበር እና አንድነት በማረጋገጥ የማይተካ ሚና ይኖረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ ጦርነትና አብዮት የተሟላ መፍትሔ የማያመጡ መሆናቸውን በተግባር የተረጋገጠ ጉዳይ ነው፡፡ በሁለቱም መንገድ የመጣ አሸናፊነት ጊዜያዊና መልሶ ቁርሾና ቂምን የሚያሳድር መንገድ መሆኑን ተምረንበታል፡፡ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት በውይይትና በምክክር ችግሮቻቸውን አለመግባባቶቻቸውን የመፍታት ድንቅ ባህል የነበራቸው ህዝቦች ናቸው፡፡ ነገር ግን ይህ እሴት እየጎለበተ በመጣው ኋላቀር የፖለቲካ ባህል ምክንያት ከጊዜ ወደጊዜ በመደብዘዝ ከፋፋይ ነጠላ ትርክት መገለጫችን እስከመሆን ደርሷል፡፡ በአለም ላይ በርካታ ሀገራት ከከረረ ልዩነትና ከግጭት ድባብ ለመውጣት ሀገራዊ ምክክር እንደመፍትሄ ተጠቅመዋል፡፡ እኛም ኢትዮጵያውያን ይህንን ማድረግ የማይሳነን ሕዝቦች ለመሆናችን በየአካባቢው ያሉ ባህላዊ ዕሴቶቻችን ማሳያ ናቸው፡፡ ስለሆነም ዘላቂ የሆነ መፍትሔን ለማምጣት በእውነተኛ ፖለቲካዊ መሻት በቅንነት ለውይይት ለሰጥቶ መቀበልና ለጋራ መፍትሔ ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት መነሳት ይኖርበታል፡፡ ኢትዮጵያውያን የመጣንበት የግጭትና የጦርነት አዙሪት በቃን የምንልበት ትክክለኛው ሰዓት አሁን ነው፡፡ ግጭት ማንንም አሸናፊ የማያደርግ የጥፋት አዙሪት ስለሆነ የሀገራዊ ምክክር ሂደትን ስኬታማ ማድረግ ፣ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ የህግ የበላይነትን ማስፈን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የምትሆን ሀገር ለመገንባትና ሁላችንንም የጋራ አሸናፊ ለማድረግ ያግዘናል፡፡ በመሆኑም ሁሉም አካል በምክክሩ በንቃት እንዲሳተፍ በዚህ አጋጣሚ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡ ምክክር ለጋራ አሸናፊነት፣ ምክክር ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገረመንግሥት ግንባታ! የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ታኅሣሥ 24/2018 ዓ.ም
ማህበራዊ
ምሁራን ጠያቂ፣ አሰላሳይና በፈተና ውስጥ አልፎ ሀገር የሚገነባ ትውልድ የማፍራት ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jan 4, 2026 98
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ ምሁራን ጠያቂ፣ አሰላሳይና ሀገር ወዳድ ትውልድ የመፍጠር እንዲሁም በፈተና ውስጥ አልፎ ሀገር የሚገነባ ትውልድ የማፍራት ኃላፊነት እንዳለባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሁፍ አቅርበዋል። በዚህም የምሁርነትን ምንነት፣ መገለጫና ተግባራዊ ሚናን አስመልክቶ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪቸውም ምሁራን ከሌላው ማኅበረሰብ የሚለዩት ባላቸው እሳቤና ተግባር መሆኑን ጠቅሰው ምሁርነት ለጥያቄ ዝግጁ መሆንና የመጠየቅ ብቃት ነው ብለዋል፡፡ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሄድ ለምሁርነት አንድ ደረጃ ወደ ፊት የሚያስኬድ ቢሆንም እውነተኛ ምሁርነት ግን በጥያቄ ውስጥና ከጥያቄ በኋላ በሚገኝ የመጠየቅ ብቃትና ትጋት የሚለካ መሆኑን ገልጸዋል። ምሁርነት ውስብስብ ጉዳዮችን ለመዳሰስ መሞከር፣ ሐሳብን ለመናገር፣ ለማድመጥና ለመጠየቅ መዘጋጀት መሆኑን ጠቅሰው ይህም በዋናነት በማሰብ አቅም ግንባታ ላይ የሚሠራ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል። ከማሰብ አቅም ባለፈ ብልህነት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመውም ብልህነት ስሜታዊ ብልህነትን፣ ማኅበራዊ ብልህነትንና የማሰብ አቅምን የሚያቅፍ መሆኑን አብራርተዋል። ሀገሪቱ ዘመን ቀያሪና ትውልድ አሻጋሪ እሳቤዎች እንደሚያስፈልጓት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሁራን መገለጫ ሐሳብ አክባሪና አፍቃሪ፣ ጥልቅ አሰላሳይና ብዙ ጠያቂ፣ አንባቢና ነቃሽ ተንታኝ፣ እንዲሁም ችግር ፈቺና መፍትሔ አሳሽ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል። ምሁራን ነገሮችን ከተለመደው መንገድ በተለየ መልኩ የማየት፣ ውስብስብ ጉዳዮችን የመተንተንና ዕውቀትን ወደ ሚጨበጥ ተግባር የመቀየር ብቃት ሊኖራቸው እንደሚገባም አክለዋል። ምሁራን ትውልዳዊ፣ ማኅበረሰባዊ፣ ኢንዱስትሪያላዊና ዓለም አቀፋዊ ሚናዎች እንዳሏቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጠቁመዋል። ምሁራን ጠያቂ፣ አሰላሳይና ሀገር ወዳድ ትውልድ የመፍጠር እንዲሁም በፈተና ውስጥ አልፎ ሀገር የሚገነባ ትውልድ የማፍራት ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ማኅበረሰቡን ከማንቃት ባለፈ፣ በምርምር የተገኙና በሰነድ ተቀምጠው የቆዩ የፈጠራ ንድፎችን ወደ ተግባር መቀየር እንደሚገባቸውም ነው የተናገሩት። የምሁራንን ተግባራዊ ሚና በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚመደቡ ጠቁመው የዕውቀት ዘር መዝራት፣ የለውጥ አቅጣጫ መቀየስ እና የወል እሴትን መበየን መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ምሁር ከቀደምቶችና ከታሪክ የተገኘውን ዕውቀት ለዘመኑ በሚመጥን መልኩ ቅርጽ ማስያዝ፣ መከራከርና ዕውቀቱ ዓለም አቀፋዊ እንዲሆን ማድረግ ይገባዋልም ነው ያሉት። የፈጠራ፣ የሥራ፣ የዴሞክራሲ፣ የሲቪክና የጽዱ ከተማ ባህልን የሚያጎለብቱ ሐሳቦችንና እሴቶችን መፍጠር እንዲሁም ለውጥን መተግበር የሚያስችሉ የጋራ እሴቶችን መቅረጽ አለባቸው ብለዋል፡፡ ምሁራን ሥርዓታዊ፣ ስልታዊ፣ ፈጠራዊና አመክንዮአዊ እሳቤዎች ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባቸው አስገንዝበው ምሁራን ለሁሉም እሳቤዎች አስኳል መሆናቸውን ተናግረዋል።
የገዳ ስርአት እሴቶችን በማስረጽ በህዝቡ ውስጥ ሰላምና አብሮነት እንዲጎለብት እየተሰራ ነው
Jan 4, 2026 73
መተሓራ ፤ታህሳስ 26/2018 (ኢዜአ):- የገዳ ስርአት እሴቶችን በማስረጽ በህዝቡ ውስጥ ሰላምና አብሮነት እንዲጎለብት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ። ትውልዱ የገዳ ስርአት እሴቶችን በመጠበቅ ለአብሮነት እና አንድነት መጽናት የበኩሉን መወጣት እንዳለበት ተመላክቷል። የከረዩ ሚችሌ ገዳ ስልጣኑን ወደ ሀልችሳ የጎባ የሚያስረክብበት የስልጣን ርክክብ ስርዓት ‘ቡታ ቀሉ’ መርሃ ግብር በምስራቅ ሸዋ ዞን መተሃራ አካባቢ ተሬ ሌዲ በተባለ ስፍራ እየተካሄደ ይገኛል። የሚችሌ አባ ገዳ ቡላ ዲዶ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት በጥንታዊ የገዳ ስርዓት መሰረት ህዝቡ በሰላም አብሮ እንዲኖር ሚናቸውን ሲወጡ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የገዳ ስርዓት እሴቶች ሰላምን ማጽናት እና የህዝቡን አብሮነት የሚያጠናክሩ ለጋራ ልማት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ናቸው ብለዋል። በቀጣይም ትውልዱ ባህሉን በመጠበቅ አብሮነትንና አንድነትን ለማጽናት ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በተለይም ባለፉት ዓመታት የገዳ ስርአት እሴትን በማስተማር በህዝቡ ውስጥ ሰላምና አንድነት እንዲጎለብት መሰራቱን ጠቅሰዋል። ትውልዱ በገዳ ስርዓት እሴት በመታነፅ ከመጤ ባህል ተጽእኖ ራሱን እንዲጠብቅ ለማስቻል እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የቦረና ኦሮሞ ባህልና ታሪክ ተመራማሪ የሆኑት አቶ ገልማ ጎሎ ዳባ በበኩላቸው የገዳ ስርዓት በርካታ ጠቃሚ እሴቶች ያሉት ነው ብለዋል። ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት መሰረት የሆነው የገዳ ስርዓት አብሮነት እና አንድነትን የሚያጸና በመሆኑ በትውልዱ ሊጠበቅ እንደሚገባ አስረድተዋል። የገዳ ስርአት ለትውልድ እንዲተላለፍ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በየስምንት ዓመቱ የሚደረገው የስልጣን ርክክብ የገዳ ስርዓት እሴት እየተሸጋገረ እንዲሄድ እያደረገው መሆኑን ጠቅሰዋል። ሌላው የኦሮሞ ባህልና ታሪክ ተመራማሪና መምህር የሆኑት አስሀፋ ተፈራ ( ዶ/ር) የገዳ ስርዓት ለሰላም እና አብሮነት ጠቃሚ እሴቶች እንዳሉት ጠቅሰዋል። “ስርአቱ በመጤ ባህል እንዳይበረዝ በጥናትና ምርምር የመደገፍ ስራ እየሰራን ነው “ብለዋል። ተተኪው ትውልድ ከመጤ ባህል ተጽእኖ ራሱን በመጠበቅ በገዳ ስርዓት እሴት እንዲታነጽ እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል። የህዝቡን ባህልና ቋንቋ የማልማትና የማሳደግ እንዲሁም የገዳ ስርዓት እሴት ለትውልድ እንዲተላለፍ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክተው እንደሚቀጥሉ አመላክተዋል። የከረዩ ኦሮሞ የገዳ ስልጣን ሽግግር ስነ-ስርዓት ታህሳስ 26 እና 27 ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ በድምቀት እየተካሄደ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለገና በዓል በቂ ምርት ቀርቧል
Jan 4, 2026 80
ሚዛን አማን፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለገና በዓል በቂ ምርት በመቅረቡ ግብይቱን የተረጋጋ እንዳደረገው የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ ታሪኩ አካሉ ለኢዜአ እንደገለጹት በዓሉን ምክንያት በማድረግ በቂ የምርት አቅርቦት እንዲኖር በቅንጅት ተሰርቷል፡፡ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖርና የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት የቁጥጥር ሥራ ከክልል እስከ ወረዳ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ወደ ተግባር መገባቱንም ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል የፍጆታ ምርቶች በቅዳሜና እሁድ ገበያ እንዲቀርቡ የማመቻቸት ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው የግብርና ምርቶች ገበያ ትስስር የመፍጠር ተግባርም እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል። በተደረገው ጠንካራ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ምርት በበቂ ሁኔታ መቅረቡንና በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የተረጋጋ የግብይት ሥርዓት መኖሩን ገልጸዋል። በክልሉ የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሰርካለም ወልደሰንበት ለበዓሉ የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ ወደ ገበያ መቅረባቸውን ተናግረዋል። ወይዘሮ ሙሉወርቅ ዘውዴ በበኩላቸው በዘይት፣ እንቁላልና አንዳንድ ምርቶች ላይ ቀደም ሲል ከነበረው ዋጋ እስካሁን የተለየ ጭማሪ አለመኖሩን ገልጸው በመንግሥት የሚደረገው ክትትል ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። አቶ ኢያሱ ኮብቴት የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ በበኩላቸው የእርድ እንስሳት በበቂ ሁኔታ መቅረባቸውን ተናግረዋል።
የሀላባ ዘመን መለወጫ "መንገሳ" በዓል የአብሮነት ማሳያ ነው
Jan 4, 2026 158
ሆሳዕና ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦የሀላባ ዘመን መለወጫ "መንገሳ" በዓል የአብሮነት ተምሳሌት መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመሰረት ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑሪዬ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ የሀላባ የዘመን መለወጫ መንገሳ በዓል "ሴራ ባህላችን በህብር የመቻል አቅም ማሳያችን" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ባህላዊ ስነ ስርዓቶች በሆሳዕና ከተማ ተከብሯል፡፡ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመሰረት ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑሪዬ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ የሀላባ የዘመን መለወጫ መንገሳ በዓል የብዝሃነት መገለጫ እና የአብሮነት ተምሳሌት ነው፡፡ "መንገሳ" በሀላባዎች ዘንድ የአሮጌው ዓመት ማብቂያና የአዲስ ዓመት መቀበያ ሆኖ በታህሳስ ወር ማብቂያ የሚከበር የዘመን መለወጫ በዓል መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ አርሶ አደሮች ያለሙትን ምርት በመሰብሰብ ለቀጣይ የእርሻ ወቅት ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት የሚከበር ደማቅ በዓል ነው ሲሉም ገልጸዋል። እንዲሁም ለአቅመ አዳም የደረሱ ወጣቶች ወደ አዲስ ምዕራፍና ህይወት ራሳቸውን በሚያሸጋግሩበት ወቅት የሚከበር በዓል ስለመሆኑም አክለዋል፡፡ የዞኑ ማህበረሰብ ከመንግሥት ጎን በመቆም በራስ አቅም ከተረጂነት ለመውጣት የሚያስችሉ በርካታ የልማት ስራዎች ማከናወኑን አስታውሰው፣ በራስ የመቆም እሴትን አጠናክሮ ለማስቀጠል የበዓሉ መከበር አይነተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም ገልፀዋል፡፡ የሀላባ ዞን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ መሀመድ አሚን መህዲ በበኩላቸው፤ በዓሉ አብሮነትን በማጠናከር እርስ በእርስ የመረዳዳትና የመተባበር እሴቶች እንዲጠናከሩ ሚናው ከፍ ያለ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በዓሉ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማፅናት የተጀመረውን ሀገራዊ ጥረት ለማጠናከር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ጠቅሰው፣ እሴቱን ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ የበዓሉ መከበር ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል። በበዓሉ ላይ የተገኙት የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ፤ የሀላባ ዘመን መለወጫ የሆነው "መንገሳ" በዓል በትብብርና በአብሮነት በመጓዝ ለጋራ ተጠቃሚነት መረጋገጥ ያለው ፋይዳ ተሞክሮ የሚወሰድበት በመሆኑ እሴቱን ማስቀጠል ይገባል ሲሉም ገልፀዋል፡፡ የበዓሉ ተሳታፊ ወይዘሮ እመቤት ጀማል "መንገሳ" አብሮነትን በማጠናከር ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከሌሎች ጋር በዓሉን በአብሮነት ማክበራቸው የወንድማማችነትና የእህትማማችነት እሴቶችን ለማጠናከር የተጀመረውን ሀገራዊ ጥረት ያጠናክራል ብለዋል። በበዓሉ ላይ የክልሉ፣ የሀላባና የሀድያ ዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የባህል ሽማግሌዎችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ኢኮኖሚ
ምሁራን የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የጋራ ትርክትን በመፍጠር ምሁራዊ አመራር መሥጠት አለባቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jan 4, 2026 96
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ ምሁራን ከድህነት የተላቀቀችና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የጋራ ትርክትን በመፍጠር ምሁራዊ አመራር መሥጠት እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሁፍ አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጽሁፋቸው፤ ከሀገር ብልጽግና ከፍተኛ ሚና ያለው ምሁር በዘርፉ የተሰጠውን አመራር ለይቶና አውቆ የሚያገለግል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምሁራን ከድህነት የተላቀቀችና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት የጋራ ትርክትን በመፍጠር ምሁራዊ አመራር መሥጠት አለባቸው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያን ከድህነት አዙሪት አውጥቶ ወደ ተሟላ ብልጽግና ለማሸጋገር ምሁራን ሚናቸው የጎላ መሆኑን በማንሳት፤ ውጤታማ አመራር ለመስጠት በቅድሚያ ራስን ማሸነፍ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ መሪነት የሚጀምረው ከራስ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ምሁራን በውስጣቸው ያለውን ድምጽ ለይተው ማድመጥና ድል መቀዳጀት አለባቸው ብለዋል፡፡ ምሁራን የተሰጣቸውን ኃላፊነት፣ ዕውቀትና ተጽዕኖ ተጠቅመው ውጤታማ አመራር ለመስጠት ወሳኝ ሚና እንዳላቸውም አንስተዋል፡፡ መሪነት በጊዜና በዘመን ላይ መሰልጠን መሆኑን ገልጸው፤ እያንዳንዱን ቅጽበት ለታለመለት ዓላማ ማዋል ይገባል ነው ያሉት፡፡ የምሁርነት መገለጫ ከጊዜ ጋር የሚደረግን እሽቅድምድም ሳይቀደሙና ሳያረፍዱ መገኘት መሆኑን በመጥቀስ፤ ያሉበትን ዘመን የሚረዱ ውጭውን ማየት የሚችሉ መሆን እንዳለባቸውም ገልጸዋል፡፡ ሀሳብ የለውጥ ሀይል ምሁራን ደግሞ የለውጥ ወኪል ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በፖለቲካ በኢኮኖሚ እና በሰዎች መስተጋብር የሀሳብ ውክልናቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል፡፡ ሀሳብ እንቅስቃሴ ይፈጥራል፤ እንቅስቃሴ ስርዓት ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የምሁራን ሀሳብ ተቋም መፍጠር አለበት ብለዋል፡፡
በውስጣዊ እና በራስ ዐቅም የባቡር መንገድ ግንባታ ላይ የተመዘገበው ዕድገት እጅግ የሚያስደንቅ ነው -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Jan 4, 2026 97
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ በውስጣዊ እና በራስ ዐቅም የባቡር መንገድ ግንባታ ላይ የተመዘገበው ዕድገት እጅግ የሚያስደንቅ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ ወደ የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር አ.ማ ጉብኝት አድርገናል ብለዋል። ጉብኝቱ የሀገራችንን ብሔራዊ የሎጂስቲክስ ክዋኔ ዐቅም ለመገምገም እና የሀገሪቱን እያደገ ያለ የልማት አጀንዳ ለመደገፍ በሎጂስቲክስ ዝግጁነት ላይ ገንቢ ውይይቶችን ለማካሄድ ጠቃሚ ዕድል ሰጥቶናል። ኢኮኖሚያችን እያደገ ሲሄድ የሎጂስቲክስ ዘርፉ ካልዘመነ ዘላቂ ዕድገትን የሚገድብ ዋና መሰናክል መሆኑን ይቀጥላል ብለዋል። አሁን በተለይ በውስጣዊ እና በራስ ዐቅም የባቡር መንገድ ግንባታ ላይ የተመዘገበው ዕድገት እጅግ የሚያስደንቅ መሆኑንም ገልጸዋል። ይህም የሀገር ውስጥ ዐቅምን ለመገንባት፣ ውጤታማነትን ለማሻሻል እና በባቡር ዘርፍ ውስጥ ረጅም ጊዜ የሚቆይ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። ሎጂስቲክስ ከባሕር እስከ መጋዘኖች ድረስ ያለውን ሙሉ ሰንሰለት እንደሚያካትት ገልጸው፤ ይህም ወደቦች፣ የባቡር መንገዶች፣ አውራ ጎዳናዎች፣ የትራንስፖርት አገልግሎቶች እና የማከማቻ ተቋማትን እንደሚጨምር ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅትም በእጃችን ውስጥ ባሉ መስኮች ላይ እንደ ደረቅ ወደቦች፣ የባቡር መሠረተ ልማት፣ አውራ ጎዳናዎች እና የመጋዘን ግንባታ አስፈላጊ ማሻሻያዎችና ዘመናዊ የማድርግ ሥራዎች በሂደት ላይ ናቸው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት እነዚህን ተያያዥ የሎጂስቲክስ ክፍተቶችን በተቀናጀ መንገድ መፍታት የዘርፉን መሰናክሎች ለመሻር እና የሀገሪቱን ሰፊ የልማት ግቦች ለመደገፍ ወሳኝ ይሆናል።
አሲዳማ አፈርን ማከሚያ አማራጮችን በማስፋት ምርታማነትን ለማሳደግ የተሰራው ሥራ ውጤታማ ነው
Jan 4, 2026 103
ዲላ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ አሲዳማ አፈርን ማከሚያ አማራጮችን በማስፋት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተከናወነ ባለ ሥራ ውጤት መገኘቱን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለጸ። በጌዴኦ ዞን ቡሌ ወረዳ ‹‹ኦሲ ማሳ›› በተሰኘ ምጥን ማዳበሪያ በታከመ 13 ነጥብ 5 ሄክታር ኩታ ገጠም መሬት ላይ ለሰርቶ መሳያ በለማ የምግብ ገብስ ምልከታ ተካሂዷል። በመስክ ምልከታው ኦሲ ማሳ ከኖራ በአማራጭነት አሲዳማ መሬትን በማከም የሰብል ምርታማነትን ለማረጋገጥ ማስቻሉ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የግብርና ኤክስቴንሽን ዳይሬክተር አዲሱ በዛብህ(ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማውጣት በሰርቶ ማሳያ ወደ አርሶ አደሩ እያስፋፋ ነው። አርሶ አደሩ ቴክኖሎጂዎችን ተቀብሎ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ቢያደርግም የአፈር አሲዳማነት በውጤታማነቱ ላይ ጫና እያሳደረ ነው ብለዋል። ኖራንና የተፈጥሮ ማዳበሪያን ተጠቅሞ አሲዳማ አፈርን ማከሚያ አማራጮችን በማስፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አንስተው፣ ለዚህም ኦሲ ማሳ ምጥን ማዳበሪያ አማራጭ መፍትሄ መሆኑን ገልጸዋል። የኦሲ ማሳ ምጥን ማዳበሪያን ጥራትና ዘላቂ ውጤታማነትን ከማረጋገጥ ባለፈ ተደራሽነቱን ለማስፋት ትኩረት መደረጉን ያነሱት ደግሞ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወንዳለ ሃብታሙ(ዶ/ር) ናቸው። ይህም ግብርናን በማዘመን ሽግግር ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ በመሆኑ በየደረጃው ቅንጅታዊ አሰራሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል። የወንዶ ገነት ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ሄኖክ ተስፋዬ በበኩላቸው ኦሲ ማሳ ምጥን ማዳበሪያ አሲዳማ አፈርን በማከም የሰብል ምርታማነትን ማረጋገጥ የሚስችል ነው ብለዋል። ምጥን ማዳበሪያውን ባለፉት ሦስት ዓመታት በኩታ ገጠም የአርሶ አደር ማሳ ተሞክሮ ውጤታማነቱ በመረጋገጡ በአሁኑ ወቅት ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በቡሌ ወረዳ በሰብል ከተሸፈነው 12ሺህ ሄክታር ማሳ ውስጥ ከ3ሺህ 800 የሚልቀው በአሲዳማነት የተጠቃ በመሆኑ ምርታማነት ላይ ጫና መፍጠሩን ያነሱት ደግሞ የቡሌ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አበበ ሽፈራው ናቸው። ችግሩን ለመፍታት ከተለያዩ የምርምር ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በተለይ የኦሲ ማሳ ምጥን ማዳበሪያ ችግሩን እያቃለለ መሆኑን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅት በ13 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ ተሞክሮ ውጤታማ መሆኑንና ወደ 140 ሄክታር በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በአማራ ክልል ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተመዘገበ ነው
Jan 4, 2026 93
ደብረ ብርሃን፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግና የሀብት አጠቃቀምን በማሻሻል ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተመዘገበ መሆኑ ተገለጸ። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ በአምስተኛው ዙር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የተሸጋገሩ ከ630 ሺህ በላይ የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎችን ዛሬ አስመርቋል። በምረቃው ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ተረጂነት ብሔራዊ ክብርን የሚነካ በመሆኑ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥና መጠባበቂያ ፈንድ በማከማቸት እርስ በእርስ የመደጋገፍ ባህልን ለመገንባት ትኩረት ተሰጥቷል። በሁሉም ዘርፎች ምርታማነትን በማሳደግና የሀብት አጠቃቀምን በማሻሻል ከተረጂነት ወደምርታማነት ለመሸጋጋር ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንና በዚህም ውጤት እየተገኘ መምጣቱን ተናግረዋል። ዛሬ ለምረቃ የበቁ ዜጎች እለቱ ከተረጂነት እንደወጡ ያወጁበት ቀን እንደሆነ ተረድተው በቀጣይ በተሰማሩበት መስክ ውጤታማነትን ማስቀጠል እንዳለባቸው ገልጸው፣ በክልሉ ተረጂነትን ታሪክ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ኢያሱ ኤልያስ በበኩላቸው እንዳሉት፤ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ስራን በማጠናከር ዜጎችን ከተረጂነት ለማላቀቅ እየተሰራ ነው። በአማራ ክልል ተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራን ማስፋትና ማጠናከር ከተቻለ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከድህነት መውጣት እንደሚቻል የዛሬ ተመራቂዎች ተግባር ማሳያ ነው ሲሉም ገልጸዋል። የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ደረጀ ማንደፍሮ፤ በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራሙ በክልሉ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ፣ የደን ልማት እና እንክብካቤ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። በዚህም የአፈር መከለትን ከመከላከል ባለፈ መሬቱ እንዲያገግም በማድረግ ለልማትና ለጥቅም እንዲውል መደረጉን ጠቁመዋል። አነስተኛ የመስኖ አውታር በመገንባት አርሶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት እንዲላቀቅ በመደረጉም ምርትና ምርታማነት ከመጨመሩ ባለፈ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መቻሉን አስረድተዋል። እንዲሁም የአርሶ አደሩን የገንዘብ ቁጠባ፣ አያያዝና አጠቃቀም ክህሎትን በማሳደግ የገጠሩ ማህበረሰብ የባንክ አጠቃቀም ስርአቱ እንዲሻሻል ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። ዛሬ የተመረቁት 630 ሺህ 472 ዜጎች ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የተሸጋገሩና የምግብ ዋስትናቸውን ያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በክልሉ ዜጎች ከጠባቂነት እንዲላቀቁ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ ፤ በዞኑ ልማትን በማፋጠን የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የተፈጥሮ ጸጋዎች እንዳሉ ተናግረዋል። በለውጡ መንግስት ራስን ለመቻል በተሰራው ስራ ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር የተጀመሩ ስራዎች እየተጠናከሩ መምጣታቸውን ገልጸዋል። ከዛሬ ተመራቂዎች መካከል ከመንዝ ጌራ ወረዳ አርሶ አደር ዘመድኩን ወረደ፤ በሴፍቲኔት ፕሮግራም ሰርቶ ሀብት ማፍራት ብቻ ሳይሆን የአሰራር ባህልንም ተምሬያለሁ ብለዋል። በፕሮግራሙ ከታቀፉ በኋላ ጥንድ የእርሻ በሬ፣ ላሞች እና ከ35 በላይ በጎችን ማፍራት ከመቻል ባለፈ የራሳቸውን መኖሪያ ቤት ለመገንባት መቻላቸውን ገልጸዋል። ከአንጎለላና ጠራ ወረዳ አርሶ አደር ግዛው ሰለሞን ፤ በፕሮግራሙ ከመታቀፋቸው በፊት በአስከፊ ድህነት ውስጥ ይኖሩ እንደነበር አስታውሰዋል። በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ባከናወኑት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የእንስሳት እርባታ ሥራዎች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል። በዛሬው እለት እንደ ክልል በደብረ ብርሀን ከተማ የተመረቁትን ጨምሮ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች፣ ዞኖችና ወረዳዎች የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ተመርቀው ወደ ምርታማነት መሸጋገራቸው ታውቋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የዲጂታል ሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አንድ ሰው አንድ ማንነት እንዲኖረው ያስችላል
Jan 4, 2026 95
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦የዲጂታል ሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አንድ ሰው አንድ ማንነት እንዲኖረው በማድረግ ትክክለኛ ፖሊሲ መቅረጽ የሚያስችል መሆኑን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ገለጸ፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በአዋጅ ቁጥር 1370/2017 መሰረት ከፌደራል እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን ድረስ ራሱን የቻለ አደረጃጀት ያለው ሆኖ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የማከናወን፣ የመምራት፣ የማስተባበር፣ የመደገፍ፣ የምዝገባ መረጃዎችን የማስተዳደር እና የማደራጀት፣ በብሔራዊ ደረጃ በመረጃ ቋት አደራጅቶ የመያዝ ሀላፊነት ተሰጥቶታል። አገልግሎቱ በተሰጠው ስልጣን መሰረተ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ውክልና በመስጠት በመዲናዋ ሁሉም ወረዳዎች የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ማከናወን ጀምሯል፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቢቂላ መዝገቡ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የወረቀት አሰራርን በመቀየር አንድ ሰው አንድ ማንነት እንዲኖረው ያደርጋል፡፡ ከዚህ ቀደም በነበረው የማኑዋል/የወረቀት አሰራር አንድ ሰው ሁለት ቦታ የልደት፣ የሞትና መሰል የወሳኝ ሁነት የምስክር ወረቀት ያወጣ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በዚህም በተጭበረበረ መረጃ የተሰሩ የወሳኝ ሁነት መረጃዎች መንግስት ለሚያሳልፋቸው የፖሊሲ ውሳኔዎች አስቸጋሪ ሆነው መቆየታቸውን ገልጸዋል፡፡ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የባዮሜትሪክና ባዮግራፊክ መረጃ እንደሚይዝ ገልጸው፤ የባዮሜትሪክ መረጃዎችን ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር እንዲተሳሰር ይደረጋል ብለዋል፡፡ በዚህም አንድ ሰው አንድ ሆኖ የሚታወቅባትን ኢትዮጵያ መፍጠር የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የባዮሜትሪክና ባዮግራፊክ መረጃዎችን በማቀናጀት የአንድን ሰው ትክክለኛ ማንነት የሚገልጹ መሆናቸውን የገለጹት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ የአንድን ሰው ዜግነት መለየትም ያስችላሉ ብለዋል፡፡ እነዚህ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ መረጃዎችን በኩነት ምዝገባና እና በብሄራዊ መታወቂያ /ፋይዳ/ አማካኝነት መሰብሰብ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ማከናወን የሚያስችል መተግበሪያ በኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አማካኝነት ለምቶ ወደ ሥራ መግባቱንም ተናግረዋል፡፡
የዲጂታል ግብይት ሥርዓት የንግድ እንቅስቃሴን አቀላጥፏል
Jan 4, 2026 62
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እያደገ የመጣው የዲጂታል ግብይት ሥርዓት የንግድ እንቅስቃሴን ከማቀላጠፍ ባለፈ ከመጭበርበርና ከእንግልት እየታደጋቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ መጪዎቹን የገና እና የጥምቀት በዓላት ግብይታቸውን በቴሌብር እና በሞባይል ባንኪንግ በመጠቀም ያለምንም እንግልት እያከናወኑ መሆኑን ለኢዜአ ተናግረዋል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት መካከል አቶ ገዛህኝ መካሻ እንደገለጹት፤ የዲጂታል ግብይት ሥርዓቱ በፈጠረው ምቹ ሁኔታ ማንኛውንም ክፍያ በቴሌብርና በሞባይል ባንኪንግ እንደሚፈጽሙ ገልጸዋል። ይህም ጉልበትንና ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ፣ ተንቀሳቃሽ ገንዘብ በመያዝ ከሚገጥሙ ስጋቶችና ከአጭበርባሪዎች ራሳቸውን ለመከላከል እንዳስቻላቸው ጠቁመዋል። በመሆኑም ለመጪዎቹ በዓላት የሚገዟቸውን ቁሳቁሶች በዲጂታል መንገድ እየፈጸሙ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ዶክተር ሳሮን ሲሳይ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል የነበሩ የክፍያ አገልግሎቶች በእንግልት የተሞሉና ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም የማይመቹ እንደነበሩ አስታውሰዋል። አሁን ላይ ግን እያንዳንዱን አገልግሎት በዲጂታል መንገድ መፈጸም መቻሉ ሕይወትን በእጅጉ ቀለል እንዳደረገው ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እያሳየች ያለውን ፈጣን ዕድገት ለማስቀጠል የዲጂታል ዓለምን መቀላቀሏ የሚያስደስት መሆኑን የገለጹት ደግሞ መምህርት ፍሬሕይወት ለማ ናቸው። የዲጂታል ግብይት ሥርዓቱ ጥሬ ገንዘብ የመያዝ ልማዴን በማስቀረት ሁሉንም አገልግሎት በስልኬ እንዳገኝ አስችሎኛል ሲሉም አክለዋል። የኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል መኒ ቢዝነስ ዋና ኦፊሰር አቶ ብሩክ አድሃና፤ ተቋሙ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የዲጂታል ሕልም እውን ለማድረግ በትጋት እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ኦፊሰሩ ገለጻ፤ባለፉት አራት ዓመታት ከሀምሳ ሰባት ሚሊዮን በላይ በሆኑ የዲጂታል ክፍያ ደንበኞች አማካኝነት ከስድስት ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት ተከናውኗል። መጪዎቹን የገናና የጥምቀት በዓላት ምክንያት በማድረግም ደንበኞች የዲጂታል ግብይቶችንም ሆነ ሌሎች አገልግሎቶችን ያለምንም መቆራረጥ እንዲያከናውኑ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን አረጋግጠዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለትምህርት ጥራትና ተደራሽነት መረጋገጥ የላቀ ሚና ይጫወታል
Jan 4, 2026 63
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ለትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ይበልጥ መረጋገጥ የላቀ ሚና እንደሚጫወት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ ገለጹ፡፡ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ፤ ጥራት ያለውና ፍትሐዊ የትምህርት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂን አማራጮች በአግባቡ መጠቀም ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ ዓለም አቀፋዊውን የዕድገት ፍጥነት ተከትሎ በትምህርት መስኩ ዕውቀትና ክህሎቱ የዳበረ ማኅበረሰብን ለመፍጠር ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ጉልህ አሻራ አሳርፏል ነው ያሉት። በተለይም የመማር ማስተማር ሂደቱን በማዘመንና የፈተና አሰጣጥ ሥርዓቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ የፈተና ደኅንነት እንዲጠበቅ ማድረጉንም ገልጸዋል፡፡ ስትራቴጂው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሀገሪቱን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ የሚደግፉ የሥልጠና መስኮችን እንዲከፍቱና በዘርፉ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የሚያስችሉ ግብዓቶች እንዲሟሉ ምቹ መደላድል መፍጠሩንም አክለዋል። መንግሥት የሀገሪቱን ብልጽግና ለማረጋገጥ የጀመረውን የማዘመን ሥራ ይበልጥ ለማሳለጥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ተግባራዊ ማድረጉንም ገልጸዋል፡፡ ይህ ስትራቴጂ ዜጎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ አማራጮች ታግዘው ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲማሩ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ስትራቴጂው የትምህርት ተደራሽነትን ከጥራት ጋር በማጣመር ረገድም የላቀ ፋይዳ እንደሚኖረው ጠቁመዋል፡፡ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራትና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ከኢንዱስትሪው ጋር ይበልጥ ለማቀራረብ በትኩረት ይሠራል ብለዋል፡፡ ይህም ተማሪዎች በቴክኖሎጂው ረገድ ተግባር ተኮር ዕውቀትና ክህሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። በተጨማሪም በዲጂታላይዜሽን ዙሪያ የሚከናወኑ የምርምር ውጤቶች ለተግባራዊ ጥቅም እንዲውሉ በማድረግ የትምህርት ዘርፉ ለስትራቴጂው ስኬት የሚጠበቅበትን ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል።
ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬታማነት ቁልፍ ሚና አለው
Jan 4, 2026 71
ጅግጅጋ፤ ታህሳስ 26/2018(ኢዜአ)፦ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬታማነት ቁልፍ ሚናን የሚጫወት መሆኑን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያስለሴ ገለጹ። የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም 2ኛው ዙር "ፋይዳ ለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሐሳብ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በጅግጅጋ ከተማ ተካሄዷል። በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሄ አርአያስለሴ እንደገለጹት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬታማነትም ቁልፍ ሚናን የሚጫወት ነው። ዜጎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በመውሰድ የዜግነት መብታቸውን መጠቀም እንዳለባቸውም ጥሪ አስተላልፈዋል። የሱማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን፤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለሀገር ዕድገት ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸው በክልሉ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ ለዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አስፈላጊ በመሆኑ ሁሉም ዜጋ እንዲወስድ ሃላፊው አሳስበዋል። የዛሬው የሩጫ ውድድርም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሂደትን ከማነቃቃት ባለፈ በስፖርት ተወዳዳሪ ወጣቶችን ለማፍራት ትልቅ ዕድል መሆኑን አንስተዋል። በጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሩ የክልሉ አመራሮች፣ አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አትሌቶች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ስፖርት
በተጠባቂው ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ እና ቼልሲ አቻ ተለያዩ
Jan 4, 2026 87
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ20ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንችስተር ሲቲ እና ቼልሲ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቋል። ማምሻውን በኢትሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቲጃኒ ራይንደርስ በ42ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ማንችስተር ሲቲን መሪ አድርጓል። ኢንዞ ፈርናንዴዝ በ94ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ባሳረፈው ግብ ቼልሲ አቻ ወጥቷል። ባለሜዳው ማንችስተር ሲቲ በኳስ ቁጥጥር እና ኢላማ የጠበቁ ሙከራዎችን በማድረግ የተሻለ ነበር። ውጤቱን ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ በ42 ነጥብ ደረጃውን ከሶስተኛ ወደ ሁለተኛ ከፍ አድርጓል። ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ወደ ስድስት ከፍ ብሏል። ቼልሲ በ31 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል። ዛሬ በተደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ሊድስ ዩናይትድ አንድ አቻ ሲለያይ፣ የፉልሃም እና ሊቨርፑል ጨዋታ ሁለት አቻ ተጠናቋል። ብሬንትፎርድ ኤቨርተንን 4 ለ 2፣ ኒውካስትል ዩናይትድ ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 0 አሸንፈዋል። ቶተንሃም ሆትስፐርስ እና ሰንደርላንድ አንድ አቻ ተለያይተዋል። የዛሬ ጨዋታዎችን ተከትሎ የ20ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የ21ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳሉ።
ሲዳማ ቡና ሀድያ ሆሳዕናን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ
Jan 4, 2026 66
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ሲዳማ ቡና ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 0 አሸንፏል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ መስፍን ታፈሰ እና ዮሴፍ ዮሐንስ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በውድድር ዓመቱ ስምንተኛ ድሉን ያስመዘገበው ሲዳማ ቡና በ28 ነጥብ መሪነቱን አጠናክሯል። ከሶስት ተከታታይ ድሎች በኋላ ሽንፈት ያስተናገደው ሀድያ ሆሳዕና በ16 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። በሌሎች ጨዋታዎች ምድረገነት ሽሬ ኢትዮጵያ ቡናን 3 ለ 1 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሽመክት ጉግሳ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ዳንኤል ዳርጌ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። አቡበከር አዳሙ በፍጹም ቅጣት ምት ለኢትዮጵያ ቡና ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ሸገር ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ዳዊት ካሳው በጨዋታ ለሸገር ከተማ በጨዋታ፣ አዲስ ግደይ በፍጹም ቅጣት ምት ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ነጌሌ አርሲ መቻልን 2 ለ 0 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ዳዊት ተፈሪ እና አለኝታ ማርቆስ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
አዘጋጇ ሞሮኮ ለሩብ ፍጻሜ አለፈች
Jan 4, 2026 65
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26/2018 (ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሃ ግብር ሞሮኮ ታንዛንያን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ማምሻውን በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ብራሂም ዲያዝ በ64ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ጎል ሀገሩን አሸናፊ አድርጓል። ዲያዝ በውድድሩ ላይ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ አራት ከፍ በማድረግ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መምራት ጀምሯል። የሞሮኮው ኢስማኤል ሳይባሪ በ15ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል በቪዲዮ በታገዘ ዳኝነት (ቫር) ታይቶ ከጨዋታ ውጪ በመሆኑ ተሽሯል። በጨዋታው ላይ ሞሮኮ ብልጫ ወስዳ ተጫውታለች። ውጤቱን ተከትሎ አዘጋጇ ሞሮኮ ሩብ ፍጻሜ የተቀላቀለች ሶስተኛ ሀገር ሆናለች። ሞሮኮ በሩብ ፍጻሜው ከደቡብ አፍሪካ እና ካሜሮን አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ምሽት አራት ሰዓት ላይ ደቡብ አፍሪካ ከካሜሮን በአል -መዲና ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
በፕሪሚየር ሊጉ ሽረ ምድረ ገነት ኢትዮጵያ ቡናን አሸንፏል
Jan 4, 2026 71
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 26/2018 (ኢዜአ)፡- በ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሣምንት ጨዋታ ሽረ ምድረ ገነት ኢትዮጵያ ቡናን 3 ለ 1 አሸንፏል። በአዲስ አበባ ስታዲም በተካሄደው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ፤ ዳንኤል ዳርጌ እና ሽመክት ጉግሳ (2) ባስቆጠሯቸው ግቦች ሽረ ምድረ ገነት ተጋጣሚውን ረትቷል። በአንጻሩ የኢትዮጵያ ቡናን ብቸኛ ግብ አቡበከር አዳሙ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል። እንዲሁም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደረጉት ሸገር ከተማ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ግቦቹንም ዳዊት ካሳው በጨዋታ ለሸገር ከተማ እንዲሁም አዲስ ግደይ በፍጹም ቅጣት ምት ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመረብ አሳርፈዋል። ቀደም ብሎ 7 ሠዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የ13ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ጨዋታ በዳዊት ተፈራ እና አለኝታ ማርቆስ ግቦች ነጌሌ አርሲ መቻልን 2 ለ 0 አሸንፏል።
አካባቢ ጥበቃ
በአዲስ አበባ የተገነቡ የመሠረተ ልማትና የመዝናኛ ስፍራዎችን የመንከባከብ ሥራ በልዩ ትኩረት እየተከናወነ ነው
Jan 3, 2026 130
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 25/2018(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የተገነቡ መሠረተ ልማቶችንና የመዝናኛ ስፍራዎችን የመንከባከብ ሥራ በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ገለጸ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ በኮሪደር፣ወንዝ ዳርቻና በሰው ተኮር ፕሮጀክቶች የተገነቡ የመሰረተ ልማት ተግባራት ለነዋሪዎች ምቹ ስነ ምህዳር በመፍጠር መዲናዋን ውበት እያላበሷት ይገኛል። የመዲናዋ የመሠረተ ልማትና የመዝናኛ ሥፍራዎችን በመንከባከብ ለትውልድ እንዲተላለፉ ማስቻል የሁሉም ዜጎች ኃላፊነት መሆኑ አያጠያይቅም። የአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ገዛኸኝ ዴሲሳ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የመዲናዋን ዘመናዊነት የሚያስጠብቁ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። የአዲስ አበባ ከተማን የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራት መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ጭምር ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በከተማዋ በመንገድ ጽዳት የተሰማሩ ከ10 ሺህ በላይ ሙያተኞች የሚሰበስቡትን ቆሻሻ በደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ የሽርክና ማኅበር የተደራጁ አካላት መልሰው በመጠቀም ለጽዳትና ውበት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው ብለዋል። የአዲስ አበባን ውበትና ጽዳት የመጠበቅ ሥራ መዲናዋን ለቱሪዝም ፍሰትና ለነዋሪዎች እንቅስቃሴ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል። ይህም በመዲናዋ የተገነቡ የመሠረተ ልማትና የመዝናኛ ሥፍራዎችን የመጠበቅና የመንከባከብ ተግባር በልዩ ትኩረት መከናወኑ ማሳያ እንደሆነ አብራርተዋል። በቀጣይም አዲስ አበባን ምርጥ የአፍሪካ መዲና ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ጽዳትና ውበትን የመጠበቅ ሥራ በልዩ ትኩረት እንደሚከናወን አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ከተማን የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት ለማዘን የተከናወኑ የአሰራር ማሻሻያዎችም ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውል በማስቻል ገንቢ ሚና መወጣቱን አስረድተዋል። ይህም መዲናዋን ውብና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ ለተጀመረው ጥረት ስኬታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከት እያስቻለ መሆኑን ጠቅሰዋል። የመዲናዋ ነዋሪዎችም የአዲስ አበባን ውበትና ጽዳት ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት የተገነቡ መሠረተ ልማቶችን በመጠበቅና በቆሻሻ አወጋገድ ላይ ገንቢ ሚና ሊወጡ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በኢሉባቦር ዞን በ257 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ይከናወናሉ
Jan 3, 2026 93
መቱ፤ ታህሳስ 25/2018 (ኢዜአ) ፡-በኢሉባቦር ዞን በበጋው ወቅት የተፋሰስ ልማት በ257 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች እንደሚከናወኑ የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። የኢሉባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አወል መሐመድ ለኢዜአ እንደተናገሩት ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የተጎዱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ፣ የከርሰ ምድርና ገጸ-ምድር ውሀ ሀብት እንዲጎለብት በማድረጋቸው ምርታማነት እንዲጨምር አድርጓል። የተከናወኑ የልማት ስራዎችም የተራቆቱ አካባቢዎች ወደ አረንጓዴነት እንዲመለሱ በማድረጋቸው የደን ሽፋኑ መጨመሩን ገልጸዋል። ተግባሩን በማስቀጠልም ለዘንድሮው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት በተለዩ 257 ተፋሰሶች የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ይከናወናሉ ብለዋል። ስራውንም ለማሳካት ከ300 ሺህ በላይ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ 131 ሺህ ሔክታር መሬት ለማልማት ዝግጅት መጠናቀቁን ጠቁመዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ በጎርፍ የተጎዳ መሬት ለምነቱ እንዲመለስ በማድረጉ የአርሶ አደሩ ምርታማነት ማደጉን አስታውሰዋል። ባለፉት ዓመታት የተገኙ ተሞክሮዎችን በማስቀጠል በዚህ ዓመት በትጋት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን የዞኑ አርሶ አደሮች ተናግረዋል። በተቀናጀ የተፋሰስ ስራው ለመሳተፍ ከተዘጋጁ አርሶ አደሮች መካከል የበቾ ወረዳ በኮጂ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አብዱ ሱጳ ባለፉት ዓመታት የተሰሩ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ቀደም ሲል በጎርፍ ይጠረግ የነበረ መሬታቸውን ለምነቱ እንዲመለስ በማድረጉ ምርታማነታቸው ማደጉን አንስተዋል። ከዚህ ባለፈም የጠፉ ምንጮች መልሰው በማገገማቸው በበጋ ወራት በመስኖ ልማት በመሰማራት ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እንዳገዛቸው ተናግረዋል። የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ጠቀሜታን በተግባር በማየታቸው በዘንድሮው ዓመት በሚከናወነው የልማት ስራም በንቃት እንደሚሳተፉ አክለዋል። ከዚህ ቀደም በተሰሩት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የአካባቢያቸው ልምላሜ በመመለሱና የውሃ አማራጮች በመስፋታቸው ምርታማነታቸው መጨመሩን የገለጹት ደግሞ የዚሁ ወረዳ ነዋሪ አቶ ታሪኩ አየለ ናቸው። የተፋሰስ ልማቱ የተጎዱ አካባቢዎችን እንዲያገግሙ በማድረጉ ህብረተሰቡን ጭምር በመቀስቀስ በስራው በነቂስ እንዲሳተፉ እንደሚሰሩም ተናግረዋል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበጋው ደረቅ፣ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ቀጣይነት ይኖረዋል
Jan 2, 2026 159
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 24/2018(ኢዜአ)፦በሚቀጥሉት አስር ቀናት የበጋው ደረቅ፣ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ቀጣይነት እንዳለው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሰሜን፣ ምስራቅ፣ መካከለኛውና ደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ ከአምስት ዲግሪ ሴልሺየስ በታች እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ። ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ አገራችን የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ እንደሚቀጥል አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል። በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል። በሌላ በኩል ከሚጠናከሩ ዝናብ ሰጪ የሚቲዎሮሎጂ ክስተቶች ላይ በመነሳት በደቡብ ምዕራብ፣ምዕራብ፣ሰሜን ምስራቅና መካከለኛው የአገሪቱ ክፍሎች አልፎ አልፎ በጥቂት ቦታዎች ላይ አነስተኛ ዝናብ እንደሚኖር አስታውቋል። ዝናብ ሰጪ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የአገሪቱ ክፍሎች የተሻለ ገጽታ እንደሚኖረውም ገልጿል። በአብዛኛዎቹ የመኸር አብቃይ አካባቢዎች ላይ ደረቃማ የእርጥበት ሁኔታ የሚጠበቅ ሲሆን በተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ወቅቱን ያልጠበቀ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ ሊዘንብ እንደሚችል የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ አስታውቋል። የሚኖረው የበጋው ደረቅ የእርጥበት ሁኔታ በመከናወን ላይ ለሚገኘው የድህረ ሰብል ስብሰባ ስራዎች አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር ይጠበቃል ብሏል። በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት በጥቂት የደቡብ እና የደቡብ ምስራቅ የአገሪቱ አካባቢዎች አነስተኛ መጠን ያለው እርጥበት እንደሚያገኙ ጠቁሟል። የደቡብ እና የደቡብ ምስራቅ በሚገኙ ተፋሰሶች በሚቀጥሉት አስር ቀናት የተሻለ የገጸ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖራቸው ይጠበቃል ብሏል። በሌላ በኩል የተቀሩት አብዛኛዎቹ የአገሪቱ ተፋሰሶች በበጋው ደረቅ የአየር ሁኔታ ተፅዕኖ ስር እንደሚቆዩ ይጠበቃል ሲል ኢንስቲትዩቱ ገልጿል።
የብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ አውደ ርዕዩ ምርቶቻችንን በማስተዋወቅ የተሳካ የገበያ ትስስር የፈጠርንበት ነው
Dec 31, 2025 170
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 22/2018(ኢዜአ)፦ የሁለተኛው ብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ (ግሪን ሞቢሊቲ) አውደ ርዕይና ፎረም 2025 ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ የተሳካ የገበያ ትስስር የፈጠሩበት መሆኑን ተሳታፊዎች ገለጹ። በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለአምስት ተከታታይ ቀናት የተካሄደው ሁለተኛው ብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ (ግሪን ሞቢሊቲ) አውደ ርዕይና ፎረም 2025 ተጠናቋል። የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን በአውደ ርዕዩ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፤ በፎረሙ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የተካሄዱ መድረኮች በርካታ ባለድርሻ አካላትን ማገናኘት የቻሉና ውጤታማ የመረጃ ልውውጥ የተደረገባቸው ናቸው። ኢትዮጵያዊያን በዘርፉ የላቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ባቀረቡበት መድረክ ላይ በሻጮችና ሸማቾች መካከል የጠበቀ የገበያ ትስስር መፍጠሩን ተናግረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤታማ የብክለት ቀናሽ የትራንስፖርት አገልግሎት ምኅዳርን የማስፋት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም የአረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ አውደ ርዕይው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ከማስተዋወቅ ባለፈ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ስላለው ፋይዳ የጋራ ግንዛቤ የተፈጠረበት መሆኑን ገልጸዋል። የሁለተኛው ብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ (ግሪን ሞቢሊቲ) አውደ ርዕይና ፎረም 2025 ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ መድረኩ ለቀጣይ የንግድ ሥራቸው አቅም የፈጠረ ነው። የቀርጫንሼ ግሩፕ የማኑፋክቸሪንግና አውቶሞቲቭ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ አቡበከር ይማም፤ በአውደ ርዕዩ ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ ሰፊ የገበያ ትስስር መፍጠራቸውን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይ ብክለት ቀናሽ የትራንስፖርት ተሽከርካሪ ተደራሽነትን በማስፋት የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ትልም ለማሳካት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የበላይነህ ክንዴ ሜታል ኢንጅነሪንግ የጥገና ሱፐርቫይዘር ሲሳይ በፍቃዱ በበኩላቸው፤ አውደ ርዕዩ ምርቶችቸውን ለሀገር ውስጥና ለውጭ ደንበኞቻቸው በማስተዋወቅ ልምድ ያገኙበት መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ፣ በታዳሽ ኃይል፣ በአረንጓዴ አሻራና ሌሎች መስኮች አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገው ጥረት የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመቀነስ ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ነው የተገለጸው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት፤ የአፍሪካ ህብረት የ2026 መሪ ሀሳብ ዋና የትኩረት አጀንዳ
Dec 26, 2025 473
39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ነው። መሪ ሀሳቡን ያረቀቀው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የዘንድሮው መሪ ቃል ከአጀንዳ 2063 ጋር የተቆራኘ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። ሁሉም አፍሪካዊ ንጹህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በቂ ውሃ ለመጠጥ፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና ለሌሎች ፍላጎቶቹ እንዲያገኝ የማድረግ ራዕይን ለማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል። ህብረቱ የውሃ ደህንነት እንደ አህጉር የተያዙ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን በማዕቀፎቹ አስቀምጧል። ውሃ እና ንጽህና የኢኮኖሚ እድሎችን በማስፋት፣ የስራ አጥነት ምጣኔን በመቀነስ፣ የስደቶችና ተፈናቃዮችን ጫና ለማቃለል እንዲሁም ለሰላምና ደህንነት መስፈን አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተመላክቷል። የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ህብረቱ ውሃ እና ንጽህና ለጤና፣ ለኢኮኖሚ እድገት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥና ዘላቂ የአካባቢ ምህዳር ለመፍጠር መሰረት መሆኑን የበለጠ እውቅና እንደተሰጠው አመልክቷል። ሁሉን አቀፍ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይገበር የውሃ ደህንነትን የማረጋገጥ አላማ ካለው የአፍሪካ የውሃ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው። የዘንድሮው መሪ ቃል የአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ጥረቶችን ያስተሳሰረ ድልድይ ሆኗል። በዘላቂ ልማት ግቦች ውስጥ ያለው ግብ ስድስት ከውሃ እና ንጽህና ጋር የተያያዘ ነው። ይህ ግብ እ.አ.አ በ2030 ለሁሌም ዜጋ ደህንነቱ የተረጋገጠ ውሃ አቅርቦትና የንጽህና አጠባበቅን ተደራሽ የማድረግ አላማ አለው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት በፍጥነት መስፋፋትና ውሃ በአግባቡ አለመጠቀም የውሃ ደህንነት እና ዘላቂ አቅርቦት ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። የንጽህና አጠባበቅ የአፍሪካ አንዱ ፈተና ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች መሰረታዊ የሚባል የንጽህና መጠበቂያ መሰረተ ልማቶችን አያገኙም። ይህም እንደ ኮሌራ ላሉ የውሃ ወለድ በሽታዎች መስፋፋት ምክንያት ሆኗል። የተቀናጀ የውሃ አስተዳደር ስርዓት፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ ለዘላቂ መሰረተ ልማት የሚፈሰወን መዋዕለ ንዋይን ማሳደግ፣ ውሃ በድጋሚ አጣርቶ መጠቀም፣ የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ፣ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር እና ለውሃ ደህንነት ትኩረት የሚሰጡ ፖሊሲዎችና ማዕቀፎችን በውጤታማነት መተግበር ያሉትን እድሎች በዘላቂነት ለመፍታትና ፈተናዎችን ለመቅረፍ ያስችላል። ደህንነቱ የተረጋገጠ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ላይ ያለፈውን ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የቆሸሸ ውሃ በአግባቡ ማከም፣ የንጽህና አጠባበቅ ማስፋትና የግንዛቤ ፈጠራ ስራን በስፋት ማከናወን፣ ማህበረሰብ መር የንጽህና አጠባበቅ ኢኒሼቲቮችን ትግበራ ማስፋት፣ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎችና ሀገር በቀል አቅምን መገንባት ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓትን መፍጠር ያስችላል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና ጤናማ ማህበረሰብ ግንባታ ያላቸውን ቁልፍ ሚና የሚያሳይ ነው። የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ማድረግ መሰረታዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ ለማህበረሰብ ደህንነትና የተሻለ የኑሮ ዘይቤ፣ ለአካባቢ ጥበቃና ለአፍሪካ ብልጽግና መረጋገጥ ስትራቴካዊ አቅም ናቸው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በሚካሄድበት ወቅት በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም እና 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኞች ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳሉ። ኢትዮጵያ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የአፍሪካ ጣሊያን ስብሰባን ለማዘጋጀት ብሄራዊ የዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቀን ነው - የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Dec 24, 2025 415
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ሲል የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ገለጸ። የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በኤርትራ መንግሥት አገዛዝ ደረሰብን ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ጋምቢያ(ባንጁል) የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ላቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን አድንቋል። በኤርትራ መንግስት ላይ የቀረቡትን ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክስ ተቀብሎ በመዝገብ ቁጥር 868/25 መመዝገቡን፣ የክሱ ፍሬ ነገር እና ይዘት ተቀባይነት ያለው መሆኑን እውቅና በመስጠት የኤርትራ መንግስት እንዲመልስ ክሱን መላኩን ኮሚሽኑ ማስታወቁን ገልጿል። የድርጅቱ ሊቀ-መንበር ኢብራሂም ሀሩን በመግለጫቸው እንደተናገሩት፤ የኤርትራው መንግሥት በደናክል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ህዝቦች እየፈፀመ ያለው መጠነ ሰፊ፣ ስልታዊ፣ መንግስታዊ መር እና ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በአሁኑ ወቅት እየደረሱ ነው ካሏቸው የመብት ጥሰቶች መካከልም ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ማካሄድ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት፣ በሺዎች የሚቆጠሩትን መሰወር፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ማከናወን መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰው፤ በተለይም ከ300ሺህ በላይ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማፈናቀል እና ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል፣ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋትና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን መጣስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ድርጅቱ የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ከ1993 ጀምሮ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰባቸው ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ክስ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እኤአ ጁን 04 ቀን 2025 በ122 ገጽ የተደራጀ ክስ ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የኤርትራ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን እንደገለጸላቸው ጠቁመዋል። ለክሱም ከተጠቀሙት ማስረጃዎች መካከል በድርጅቱ የተከናወነ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ግኝት፣ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝባዊ መብቶች በኤርትራ ላይ የተደረጉ ምርመራዎች፣ ግኝቶችና ማስረጃዎች፣ የመብት ጥሰት የደረሰባቸው የቀይ ባሕር አፋር ተጎጂ ወገኖች እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የተገኙ የሰብዓዊ መብት ምርመራዎችን መቅረቡን ተናግረዋል። ድርጅቱ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት መከራ ለማዳን፣ የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ድምፅ እንዲሆኑት፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡንና የኢሳያስ መንግስት ላይ ህጋዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጸንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው-ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
Dec 23, 2025 367
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እና ለረጅም ጊዜ ፀንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ኃላፊ አምባሳደር ኮንስታንሲያ አዴሊና ጋስፓራስ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቅርበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት (ዋይት ሃውስ) በተካሄደ ስነ ስርዓት የአምባሳደር ኮንስታንሲያን ሹመት በይፋ ተቀብለዋል። አምባሳደሯ በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ቢሮ ስራቸውን በይፋ ጀምረዋል። ዶናልድ ትራምፕ የአምባሳደር ኮንስታንሲያ የልዑኩ መሪ ሆኖ መመረጥ በጋራ የኢኮኖሚ እድሎች፣ በሉዓላዊ አመራር ሰጪነት እንዲሁም በሰላም እና ደህንነት ላይ የተመሰረተውን የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጽኑ አጋርነት የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በአፍሪካ ሰላም፣ ብልጽግና እና መረጋጋትን ማረጋገጥን ዋና ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የአጋርነት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኝ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት የማጠናከር ፍላጎት አላት -ተሰናባቹ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና
Dec 20, 2025 418
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ሽብርተኝነትን መዋጋትን ጨምሮ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት ለማጎልበት በጋራ መስራቷን እንደምትቀጥል ተሰናባቹ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና ገለጹ። አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ ትብብር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ያለው መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ሀገራቱ የኬንያው የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና መስራች አባት ጆሞ ኬንያታ እና ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ጊዜ አንስቶ ወዳጅነት እንደነበራቸው አውስተው ትብብሩ በከፍተኛ ደረጃ በሚደረጉ ጉብኝቶች እና ውይይቶች እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ጠንካራ አጋርነት ፈጥረው እየሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ጨምሮ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመዋጋት እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ሰላም እና ደህንነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ እና የኬንያ የንግድ ትብብር እያደገ መምጣቱን የገለጹት ተሰናባቹ አምባሳደር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብሩን አድማስ የበለጠ እንደሚያሰፋው ነው የተናገሩት። ቱሪዝም እና ንግድ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ ትስስር እንዲጎለብት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ፣ ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው የ"ላፕሴት ፕሮጀክት" እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ጨምሮ በሌሎች መሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ትስስሩን የሚያሳልጡ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባሳደር ጆርጅ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በማስመረቋ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ግድቡ በቀጣናው ሽግግርን የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1963 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ቀጣናዊ መረጋጋት እና ደህንነት ፣ ንግድ እና የመሰረት ልማት ትስስር የሀገራቱ ዋንጫ የትብብር መስኮች ናቸው።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 304
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 332
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 554
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 716
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 245
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 267
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 952
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3301
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 2846
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1813
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7633
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6115
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ወንድማማቾች በአፍሪካ ዋንጫ
Dec 29, 2025 317
የአፍሪካ ዋንጫ መልከ ብዙ ውድድር ነው። የሀገራት ተቀናቃኝነት፣ ታሪካዊ ገድሎች፣ አይረሴ የተጫዋቾች የግል ብቃት፣ ጨዋታ ወሳኝ ግቦች እና ዋንጫን ከፍ አድርጎ የማንሳት የኩራት እና የሀገር ፍቅር ስሜት መገለጫዎቹ ናቸው። ከሚቆጠሩ ግቦች እና ዋንጫዎች ባለፈ ቤተሰባዊ ገጽታ ያለው ነው። የአፍሪካ ዋንጫ በርካታ ወንድማማች ተጫዋቾች በአንድ ሀገር ማልያ ሲጫወቱ የተመለከትንባቸው አጋጣሚዎች በርካታ ናቸው። በአህጉራዊው መድረክ የ68 ዓመታት ጉዞ አብረው የተጫወቱ ወንድማቾች በዚሁ ጽሁፍ እንመለከታለን። 1. ኢታሎ እና ሉቺያኖ ቫሳሎ (ኢትዮጵያ) ኢታሎ ቫሳሎ እና ሉቺያኖ ቫሳሎ በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጫወቱ ወንድማማቾች መሆናቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1962 ባዘጋጀችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የቫሳሎ ወንድማማቾች አንድ ላይ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጫውተዋል። ሉቺያኖ በውድድሩ ላይ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ከግብጹ ባደዊ አብድል ፈታህ ጋር በጋራ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ አጠናቋል። ሉቺያኖ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ተብሎ የተመረጠ ሲሆን ይህም በውድድሩ ታሪክ የኮከብ ተጫዋችነትን ሽልማት ያገኘ የመጀመሪያው ተጫዋች እንዲሆን አስችሎታል። ኢትዮጵያ በወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳቷ የሚታወስ ነው። 2. ሆሳም እና ኢብራሂም ሀሰን (ግብጽ) ሆሳም ሀሰን እና ኢብራሂም ሀሰን በአፍሪካ ዋንጫው ስኬታማ የሚባሉ ወንድማማች ተጫዋቾች ናቸው። እ.አ.አ በ1986 ግብጽ ያስተናገደችውን 15ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና እ.አ.አ በ1998 በቡርኪናፋሶ የተካሄደውን 21ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ግብጽ ስታነሳ የቡድኑ አባላት ነበሩ። ወንድማማቾቹ የአፍሪካ ዋንጫን ሁለት ጊዜ በማንሳት ባለ ክብረ ወሰን ናቸው። የ59 ዓመቱ ሆሳም ሀሰን በአሁኑ ሰዓት የግብጽ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነው። በተጫዋችነቱ በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የምንጊዜውም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። 3. አልበርት ባዋንጋ እና ሮበርት ካዛዲ (ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ) ሁለቱ ወንድማማቾች ግብጽ እ.አ.አ በ1974 ባዘጋጀችው ዘጠነኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። በወቅቱ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ዛምቢያን በማሸነፍ ዋንጫውን ስታነሳ የታሪካዊው ድል አካል ነበሩ። 4. አንድሬ ካና ቢይክ እና ፍራንስዋ ኦማም ቢይክ (ካሜሮን) ሁለቱ ወንድማማቾች በሶስት የአፍሪካ ውድድሮች ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። ተጨዋቾቹ ለመጀመሪያ ጊዜ በአህጉራዊ መድረክ በጋራ የመሰለፍ እድል ያገኙት እ.አ.አ በ1988 በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው 16ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። እ.አ.አ በ1990 በአልጄሪያ በተካሄደው 17ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ሴኔጋል እ.አ.አ በ1992 ባዘጋጀችው 18ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በጋራ ተሰልፈዋል። ጣልያን እ.አ.አ በ1990 ባዘጋጀችው 14ኛው የዓለም ዋንጫ ከወንድማማቾቹ ታናሹ ፍራንስዋ ኦማም ቢይክ ካሜሮን አርጀንቲናን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ባስቆጠራት ጎል ሁሌም በሀገሬው ሰዎች ሲወሳ ይኖራል። 5. አንድሬ አየው እና ጆርዳን አየው (ጋና) ጋናውያኑ ወንድማሞች የአፍሪካ ዋንጫ ሲነሳ ሁሌም የሚታወሱ ተጫዋቾች ናቸው። በስድስት የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ አብረው ተሰልፈዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ አብረው የሰለፉት ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን እ.አ.አ በ2012 ባዘጋጁት 28ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነው። የአየው ወንድማማቾች እ.አ.አ በ2015 ኢኳቶሪያል ጊኒ ባዘጋጀችው 30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማንሳት ተቃርበው የነበሩ ቢሆንም በፍጻሜው በኮትዲቭዋር በመለያ ምት ተሸንፈው ህልማቸው ሳይሳካ ቀርቷል። የታዋቂው አፍሪካዊ ተጫዋች አብዲ ፔሌ ልጆች የሆኑት አንድሬ እና ጆርዳን አየው እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለመጨረሻ ጊዜ በጋራ ተሰልፈዋል። ጋና እ.አ.አ በ2008 ባዘጋጀችው 26ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ጋናዊው አጥቂ አሳሞሃ ጊያን እና ታናሽ ወንድሙ ባፎር አንድ ላይ ተጫውተዋል። በተጨማሪም በዛው ውድድር ላይ ጋናውያኑ ወንድማማቾች ሪቻርድ ኪንግስተን እና ላሪያ ጊንግስተን አብረው የመጫወት እድል አግኝተዋል። 6. ኮሎ ቱሬ እና ያያ ቱሬ (ኮትዲቭዋር) በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ስማቸው በግንባር ቀደምትነት ከሚነሱ ተጫዋቾች መካከል ኮሎ ቱሬ እና ያያ ቱሬ ይጠቀሳሉ። ወንድማማቾቹ ለመጀመሪያ ጊዜ አብረው የተሰለፉት እ.አ.አ በ2006 በግብጽ አስተናጋጅነት በተካሄደው 25ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነው። በወቅቱ ኮትዲቭዋር ለፍጻሜ ደርሳ በግብጽ ተሸንፋለች። ኢኳቶሪያል ጊኒ እ.አ.አ በ2015 ባዘጋጀችው 30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኮትዲቭዋር ጋናን በማሸነፍ ዋንጫውን ለሁለተኛ ጊዜ ስታነሳ በጋራ የድሉ ተቋዳሽ ሆነዋል። የቱሬ ወንድማማቾች ለስድስት ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫው አብረው ተጫውተዋል። 7. የሞሪታኒያ እና ዛምቢያ ወንድማማች ተጫዋቾች እ.አ.አ በ2023 ኮትዲቭዋር ባስተናገደችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሪታኒያ ብሄራዊ ቡድን ስብስብ ከሁለት ቤተሰብ በተመሳሳይ ሁለት ወንድማማቾች መሳተፋቸው የተለየ ትኩረት ስቧል። ኑህ መሐመድ አብድ እና ታናሹ ሲዲ መሐመድ አህመድ አብድ በተከላካይ እና አማካይ መስመር ላይ ተሰልፈው ተጫውተዋል። ላሚን ባ እና ኤል ሃጂ ባ ለሞሪታኒያ ብሄራዊ ቡድን በመሰለፍ መጫወት ችለዋል። ዛምቢያዊያኑ ክርስቶፈር እና ፍሊክስ ካቶንጎ እ.አ.አ በ2012 ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን በጣምራ ባዘጋጁት 28ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ዛምቢያ ኮትዲቭዋር በማሸነፍ የአፍሪካ ዋንጫን ስታነሳ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2013 ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይም በጋራ ተሰልፈው ተጫውተዋል። ዛምቢያውያኑ ወንድማማቾች ኬኔት እና ሞርዶን ማሊቶሊ እ.አ.አ በ1994 በቱኒዚያ በተካሄደው 19ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ1996 ባዘጋጀችው 20ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አንድ ላይ ተሰልፈዋል። አለን ትራኦሬ እና ኢብራሂማ ትራኦሬ (ቡርኪናፋሶ) በ30ኛው እና 31ኛው የአፍሪካ ፣ ሳምቡ ያታባሬ እና ሙስጠፋ ያታባሬ (ማሊ) በተመሳሳይ በ30ኛው እና 31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ፒተር ንዶልቩ እና አዳም ንዶልቩ (ዚምባቡዌ) በ24ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ሳሉ፣ ባቺሩ እና ታጁ (ቶጎ) በ22ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ ቾሞጎ ኦማር እና ሴዲያት ኦማር (ቤኒን) በ24ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፣ መሐመድ እና ሙሳ ካሎን (ሴራሊዮን) በ20ኛው የአፍሪካ ዋንጫ እና ሳሚር ሳሊሚና አዴል ሳሊሚ (ቱኒዚያ) በ19ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አብረው የተሰለፉ ተጫዋቾች ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫ ከተሰለፉ ወንድማማቾች መካከል ስድስቱ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳታቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስታውቋል።
የኢትዮጵያ እና የህንድ ዘመን አይሽሬ እና ድንበር ተሻጋሪ ወዳጅነት
Dec 16, 2025 682
በሙሴ መለስ (ኢዜአ) ኢትዮጵያ እና ህንድ ረጅም ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አላቸው። በዚህም የስልጣኔ እሴቶችን ይጋራሉ። ሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከፈጠሩ ከ2000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እና ህንድ ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳሽነት እንደሆነም ይወሳል። ኢትዮጵያ እና ህንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1948 ነው። እ.አ.አ በ1950 ሳርዳት ሳንት ሲንግ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያ እና ህንድ በየሀገራቱ ኤምባሲ በመክፈት የዲፕሎማሲ ትብብሩን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ገልጸዋል። ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ እ.አ.አ በ1956 እና በ1958 በህንድ ያደረጓቸው ጉብኝቶች ከኢትዮጵያ መሪዎች ጉብኝቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። እ.አ.አ 1960 ዎቹ ማብቂያ እና 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የህንድ ፕሬዝዳንቶች የነበሩት ሳርቬፓሊ ራድሃክሪሽናን እና ዛኪር ሁሴን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝቶችን አድርገዋል። እ.አ.አ በ2011 ከአንድ ዓመት በፊት ህይታቸው ያለፈው የቀድሞው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንሞሃን ሲንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝትም ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው የህንድ ፕሬዝዳንት ራም ናት ኮቪንድ እ.አ.አ በ2017 የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ በጉብኝታቸው ህንድ እና ኢትዮጵያ በንግድ፣ ኮሙኒኬሽን እና የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 15ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የሀገራቱ መሪዎች በወቅቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ የወጣቶች ክህሎት ማጎልበት እና በሕዝብ ለሕዝብ ልውውጥ ዙሪያ ትብብርን በማጠናከር ዙሪያ ተወያይተዋል። በወቅቱ ህንድ ባዘጋጀችው የሁለተኛው “Voice of Global South Summit” በተሰኘው ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተሳትፎ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲ በህንድ አጠቃላይ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈውም ነበር። የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን የደስታ መግለጫ መልዕክት በመቀበል በአዲሱ የስልጣን ዘመናቸው ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት አጋርነት እንደሚያድግ መግለጻቸውም ይታወሳል። ህንድ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላቸውን አጋርነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። በዚህም ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ትብብር ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥም ነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ያስታወቁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 20ኛው የቡድን 20 አባላት ሀገራት ጉባኤ ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ትርጉም ያለው እና ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ህንድ የቡድን 20 አባል ሀገር መሆኗ የሀገራቱን የባለብዙ ወገን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር ነው። ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ሀገራቱ የሁለትዮሽ እና የባለዙወገን ትብብራቸውን የሚያጠናክሩ ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በወቅቱ የህንድ የትምህርት፣ ንግድ፣ ልማት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የሀገራቱ ግንኙነት የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ድጋፍ ያደረገች ሲሆን በብዝሃ ወገን ማዕቀፉ ሁለቱ ሀገራት በትብብር እየሰሩም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ህንድ በተለያዩ ጊዜያት በአየር ትራንስፖርት፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ መከላከያ፣ ተደራራቢ ታክስን የማስቀረት፣ ንግድ፣ ኮሙኒኬሽን ሳይንስ፣ባህል፣ ትምህርት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መስራት የሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 2025 ኢትዮጵያ እና ህንድ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ የተፈራረሙት የሁለትዮሽ ስምምነት ቁልፍ የሚባል ነው። እ.አ.አ በ2023/24 በወጣ መረጃ የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ምጣኔ 271 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ኢትዮጵያ አተር፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቆዳ ውጤቶች እና የከበሩ ድንጋዮችን ወደ ህንድ ትልካለች። ከህንድ ደግሞ ማሽነሪዎች፣ የመድኃኒትት ምርቶች እና የብረታ ብረት ውጤቶችን በዋናነት ታስገባለች። ህንድ የኢትዮጵያ ዋንኛ የኢንቨስትመንት አጋር ከሚባሉ ሀገራት መካከል ትጠቀሳለች። ከ500 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በጨርቃ ጨርቅ፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ። ህንድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ታደርጋለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ጤና እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከሁለቱ ሀገራት አበይት የትብብር መስኮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ የጉብኝታቸው መርሃ ግብር ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶች እና የጉብኝት ልውውጦች የኢትዮጵያ እና የህንድን ግንኙነት የበለጠ የሚያጸኑ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ህንድ በታዳሽ ኃይል፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ግብርና ማቀነባበሪያን ጨምሮ በአዳዲስ መስኮች ትብብራቸውን የማጠናከር ጽኑ ፍላጎት አላቸው። የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከእርስ በእርስ ግንኙነት ባለፈ የአፍሪካ እና ህንድ እንዲሁም የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። ከ2000 ዓመት በፊት የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ጠንካራ እና ጽኑ ትብብር ተቀይሯል። በማይናወጥ መሰረት ላይም ቆሟል። የበለጠ ጥልቀቱ እየጨመረ የመጣው የሀገራቱ ግንኙነት በጋራ ብልጽግና፣ ስትራቴጂካዊ ትስስር፣ ዘላቂ ልማት እና የሀገራቱን ዜጎች ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ ቁርጠኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።