ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በሲዳማ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው
Jun 18, 2026 7
ሀዋሳ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል 49 ሺህ ተማሪዎች የስምንተኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና እየወሰዱ ነው። የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ በየነ በራሳ በሀዋሳ ከተማ ሐይቅ ዳር አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ክልላዊ ፈተናውን አስጀምረዋል፡፡ አቶ በየነ በዚህ ወቅት እንደገለጹት የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለፈተናው ለማዘጋጀት ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ለፈተናው አስፈላጊው ዘግጅት ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው፣ በዛሬው እለትም 49 ሺህ ተማሪዎች ፈተናውን በ232 ልዩ የፈተና ማዕከላት እየወሰዱ መሆኑን ገልጸዋል። ፈተናው በልዩ ማዕከላት መሰጠቱ ጤናማ የፈተና ሂደት እንዲኖር፣ ኩረጃን ለማስቀረት እና ተገቢ ክትትልና ቁጥጥር ለማድረግ ጠቀሜታ እንዳለውም ተናግረዋል።
በክልሉ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት እየተመዘገበባቸው ነው - ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ
Jun 18, 2026 16
ሐረር፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት እየተመዘገበባቸው መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ። በሐረሪ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መሰጠት ተጀምሯል። የሐረሪ ክልል በአዲሱ የፈተና ሥርዓት የተማሪዎችን የማሳለፍ ምጣኔ እና አጠቃላይ የውጤት ጥራት ለማሳደግ ልዩ ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርቶችንና የክለሳ ፕሮግራሞችን ሲተገብር ቆይቷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተሰጠ የሚገኘውን የ8ኛ ክፍል ፈተና ዛሬ ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት በክልሉ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል። በተከናወኑ ተግባራትም የተሻሉ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸው፤ በክልሉ እየታየ የሚገኘው የትምህርት ተሳትፎ፣ ጥራትና የተማሪ ውጤት የማጎልበት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ነገዎ በበኩላቸው ለፈተናው አስፈላጊው ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል ብለዋል። በክልሉ በአጠቃላይ በገጠርና በከተማ 30 የፈተና ጣቢያዎች የተዘጋጁ ሲሆን 4ሺህ 614 ተማሪዎች ፈተናውን እየወሰዱ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ትምህርት ቢሮው ተማሪዎችን ለፈተና ለማብቃትና ውጤትን ለማሻሻል በትኩረት ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል፡፡ በተለይም ተማሪዎችን ለፈተና ለማብቃት በትምህርት ቤቶች የማጠናከሪያ ትምህርትና ሞዴል ፈተና አዘጋጅቶ የመስጠትና ሌሎች ተግባራት ሲከናወኑ መቆታቸውን አስታውሰዋል፡፡
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተማሪዎች ተከታታይነት ያለው የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ውጤታማ እንዲሆኑ ተሰርቷል
Jun 18, 2026 18
አሶሳ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተማሪዎች ተከታታይነት ያለው የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ውጤታማ እንዲሆኑ መሠራቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መሰጠት መጀመሩን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል። በሀገሪቱ የተጀመረውን የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ሪፎርም ተከትሎ፣ የብሔራዊና የክልላዊ ፈተናዎች አሰጣጥ ሥርዓት ጥብቅና ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን መደረጉ ይታወሳል። ይህንን አዲስ የፈተና ሥርዓት ተማሪዎች በብቃት መወጣት እንዲችሉ፣ መደበኛውን የመማር-ማስተማር ሂደት ከማጠናከር ባለፈ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ ከትምህርት ሰዓታት ውጭ ተከታታይነት ያላቸው የክለሳና የማጠናከሪያ ፕሮግራሞችን መስጠት የክልሎች ዋነኛ ስትራቴጂ ሆኖ እየተገበረ ይገኛል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮም ካለፉት ዓመታት ጀምሮ ፍትሐዊና ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ለማድረስ በርካታ ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ተገልጿል። በተለይም ተማሪዎች በተለያዩ ማኅበራዊና አካባቢያዊ ምክንያቶች ሊያመልጧቸው የሚችሉ ትምህርቶችን ለማካካስና በተለይም የ6ኛ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን ውጤታማነት ለማሳደግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሠራ መቆየቱን ገልጿል። የቢሮው የስርዓተ ትምህርት እና ተቋማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ሙሐመድ ኡስማን ዛሬ በአቡራሞ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ፈተናውን ሲያስጀምሩ እንዳሉት፤ ተማሪዎች ተከታታይነት ያለው የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ውጤታማ እንዲሆኑ ተሰርቷል። በተለይም ቢሮው በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለፈተናው ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ጠቅሰው፥ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ሰፋፊ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል። ተማሪዎች ፈተናውን በተረጋጋ ሁኔታ እንዲፈተኑ አስፈላጊውን የስነ ልቦና እና ምክር እንደተሰጣቸውም ተናግረዋል። በዘንድሮው ዓመት በክልሉ በ313 ትምህርት ቤቶች ላይ ከ21 ሺህ በላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና እየወሰዱ ይገኛሉ ብለዋል። በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል የፈተና የእርማት ማሽን ግዢ በመፈጸሙ የፈተናውን ውጤት በአጭር ጊዜ ውስጥ በማሳወቅ ተማሪዎች ለቀጣይ የትምህርት ጊዜ ዝግጁ እንዲሆኑ ይደረጋል ነው ያሉት።
ተማሪዎችን ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ ማብቃት የተሻለ ትውልድ ለመገንባት ያግዛል
Jun 18, 2026 42
ጅግጅጋ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ ተማሪዎችን ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ በተሻለ የትምህርት ጥራት ማብቃት ሀገር ገንቢ ትውልድ ለመገንባት ያግዛል ሲሉ የሶማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ጉሌድ አህመድ አሊ ገለጹ። በሶማሌ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መሰጠት ተጀምሯል። በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ብቁ ዜጋ ለማፍራት ሰፊ የሪፎርም ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በተለይም የታችኛው የትምህርት እርከን ለተማሪዎች ቀጣይ የዕውቀት አድማስና ለተተኪው ትውልድ ሰብዕና ግንባታ ወሳኝ መሠረት በመሆኑ፣ አጠቃላይ የትምህርት ጥራቱ ትኩረት ተሰጥቶት ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከሚከናወኑ ቁልፍ ተግባራት መካከል ደግሞ ተማሪዎች በራስ መተማመናቸውን አሳድገው፣ ፈተናን በራሳቸው አቅም በመስራት የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ማስቻል ዋነኛው ነው። ዛሬ በተጀመረው የሶማሌ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናም ተማሪዎች በራሳቸው በመተማመን የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ መሰራቱ ነው የተገለጸው። ፈተናውን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢብራሂም ዑስማን እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ መሀመድ ሼክ አደን በሼክ አብዱሰላም 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው በይፋ አስጀምረዋል። የሶማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ጉሌድ አህመድ አሊ በወቅቱ እንዳሉት፤ ተማሪዎችን ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ በተሻለ የትምህርት ጥራት ማብቃት ሀገር ገንቢ ትውልድ ለመገንባት ያግዛል። ዛሬ በተጀመረው ክልል አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተናን 29 ሺህ 631 ተማሪዎች እንደሚወስዱ ገልጸው፤ ፈተናው በክልሉ 704 ትምህርት ቤቶችና በ113 የፈተና ጣቢያዎች እየተሠጠ ነው ብለዋል። የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናው ከሰኔ 11 ጀምሮ እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚሰጥም እንዲሁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ በይፋ አስጀመሩ
Jun 18, 2026 47
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የክረምቱ ወቅት ሲደርስ፣ እኛም ለወገኖቻችን የምንዘረጋው የደግነት እጅ አብሮ ይጀግናል ሲሉ ገልጸዋል። በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ ጎሮ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ ዛሬ በይፋ ማስጀመራቸውን ጠቁመዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት መርሃ-ግብር አካል በሆነው ዲዛይን መሠረት 20 ቤቶች በአካባቢው እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ሀገራችንን በጋራ ማንሳት የምንችለው አንዳችን ለሌላችን እጃችንን ስንዘረጋ ብቻ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለሆነም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በዚህ ሥራ እንዲሳተፍ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው ለመስጠትና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት የሚጥሩ አካላትን መታገል የጋራ ሃላፊነታችን ነው - የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Jun 18, 2026 72
ሀዋሳ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው ለመስጠትና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት የሚጥሩ አካላትን መታገል የጋራ ሃላፊነታችን ነው ሲሉ በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገር ብሄራዊ ጥቅም፣ ሰላምና ልማት ላይ ያላቸውን አቋምና ምልከታ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የሀገር ሰላምና ልማትን ማደናቀፍ፣ ከብሄራዊ ጥቅም በተቃራኒ መቆም በየትኛውም መመዘኛ ትክክል ያልሆነ ተግባር መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው ለመስጠትና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት የሚጥሩ ባንዳዎችን መታገል የጋራ ሃላፊነታችን ነው ብለዋል። የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራሲ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ በለጠ ሲጌቦ፤ በሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ ሰላምና ልማት ላይ ያለልዩነት የምንሰራበት የጋራ አጀንዳችንና ሀገራዊ ግዴታችን ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ለዘላቂ ልማትና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ተቀራርበንና ተደጋግፈን ለመስራት ተዘጋጅተናል ነው ያሉት። በሀሳብ የበላይነት በሰላማዊ መንገድ መታገል የማይፈልጉ እንዲሁም በባንዳነት የተሰለፉ አካላት በየትኛውም መመዘኛ ታሪካዊ ስህተት እየፈፀሙ መሆኑን ሊገነዘቡ ይገባል ብለዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው ለመስጠትና ሰላምን ለማናጋት የሚጥሩ አካላትን መታገል የጋራ ሀገራዊ ሃላፊነታችን በመሆኑ በቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ሥራ አስፈጻሚና በክልሉ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ተወካይ ወይዘሮ ሃረገወይን ዘሪሁን፤ የሰላምና የልማት ጉዳይ ለማንም የማይተው የሁላችንም ቋሚ አጀንዳ ነው ብለዋል። በመሆኑም የህዝብን ሰላምና ልማት በማደናቀፍ ሀገርን ለማፍረስ የሚጥሩ ጸረ ሰላም ሃይሎችን ድርጊት በመታገል በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስት የመገንባት ሃላፊነታችንን ለመወጣት እንሰራለን ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ የብዝሃ እምነትና ባህል ሀገር መሆኗን አስታውሰው፣ ሁልጊዜም ልዩነቶችን በነባር ባህሎችና በምክክር በመፍታት ጠንካራ መንግስትና ሃገር መገንባት ይገባናል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለመጉዳትና ሰላሟን ለማናጋት የሚደረግ ጥረት ክህደት ስለመሆኑ አንስተው ከምንም በማስቀደም ለሀገር መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) ሊቀመንበር ለገሰ ላንቃሞ በበኩላቸው፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም፣ ሰላምና ልማት አጠናክሮ ማስቀጠል የፓርቲያችን የማይናወጥ አቋም ነው ብለዋል። የውጭ ባዳዎችንና የውስጥ ባንዳዎችን የጥፋት አጀንዳ ተቀብለው ልዩነቶችን በሃይል ለመፍታት እየተንቀሳቀሱ ያሉ ጸረ ሰላም ሃይሎችን እንደሚታገሉ ገልጸው፣ በሀገር ብሔራዊ ጥቅም ላይ ልዩነት የለንም ብለዋል። ለዘመናት ሳያግባቡን የቆዩ ሀገራዊ ጉዳዮችን ለመፍታት ታሪካዊ እድል የሰጠንን ሀገራዊ ምክክር በመጠቀም ችግሮችን በምክክር በዘላቂነት መፍታትና ሀገርን ማጽናት አለብን ሲሉም ገልጸዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅቡልነት ያለው መንግሥትና ጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት መሠረት የጣለ ነው
Jun 18, 2026 88
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ቅቡልነት ያለው መንግሥትና ጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት መሠረት የጣለ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን ገለጹ። ኢትዮጵያ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበትንና 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበትን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በስኬት አካሂዳለች። ዜጎች በየምርጫ ጣቢያቸው ከማለዳ 12 ሰዓት እስከ እኩለ ሌሊት በነቂስ በመውጣት ድምጻቸውን ሰጥተዋል፡፡ የምርጫ ሒደቱን በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን እንደገለጹት፥ ምርጫው የበርካታ ፓርቲዎች ፉክክር የታየበትና በሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁም በሀገሪቱ የሰከነ የፖለቲካ ባህል እየተገነባ መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ ዓይነቱ አካሄድ በቀጣይ ለሚመሰረተው መንግስት ጠንካራ ሕዝባዊ ቅቡልነት ከመስጠቱ በላይ፣ ለተረጋጋ የፖለቲካ ሂደትና ለልማት ዋነኛ መሠረት ይሆናል ብለዋል። በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ጌትዬ ትርፌ (ዶ/ር)፥ የምርጫ ሂደቱ ከዚህ በፊት ከተካሄዱ ምርጫዎች እጅግ የተሻለ ዴሞክራሲያዊነት የታየበት መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ህብረተሰቡ ሀገርን በማስቀደም ከቅድመ ምርጫው እስከ ድህረ ምርጫ ድረስ ያሳዩት ኃላፊነት የተሞላበት እንቅስቃሴ የሚደነቅ ነው ብለዋል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት መገናኛ ብዙኃን ያለምንም ልዩነት ሁሉንም የፖለቲካ ፓርቲዎች ለማሳተፍ የነበራቸው ቁርጠኝነትም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሕዝቡ የሰከነ እንቅስቃሴ ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማስቻሉንም በመግለጽ፡፡ በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የፖሊሲና ስትራቴጂ ተመራማሪ ተመስገን ዋለልኝ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዘንድሮው ምርጫ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጹን የሰጠበት፣ ለዴሞክራሲ ባህል መዳበር ያለውን ቁርጠኝነትም በጽናቱ ያረጋገጠበት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ መብቱን የመጠቀምና የመጠበቅ ብስለቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ያሳየ ምርጫ እንደሆነም አንስተዋል። በዚህ ምርጫ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ያለምንም ጫና የመወዳደር፣ ሀሳባቸውን በነጻነት የማንጸባረቅና አማራጭ ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የማቅረብ እድል ማግኘታቸውንም ጠቅሰዋል። ምርጫው በአሳታፊነቱ፣ በፍትሐዊነቱና በተፈጠሩ ምቹ የመወዳደሪያ ምህዳሮች በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ምዕራፍ ሽግግር የተደረገበት መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ህብረትና የኢጋድ የታዛቢዎች ልዑክ ቡድን ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ የታየበት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን ማረጋገጣቸውን መግለጻቸው ይታወቃል።
ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪዎች የግንዛቤና የክህሎት ሥልጠና መስጠት ተጀመረ
Jun 18, 2026 71
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪዎች ያዘጋጀው የግንዛቤና የክህሎት ሥልጠና መስጠት ጀምሯል። በአዲስ አበባ እየተሰጠ የሚገኘው ይህ የአመካካሪዎች ሥልጠና ከዛሬ ሰኔ 11 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሰባት ቀናት እንደሚቆይ ተመላክቷል። በሥልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ እንደገለጹት፤ ይህ የሥልጠና መርሃ ግብር ልዩነቶች በምክክር የሚፈቱበት፣ በግልጽነትና በመግባባት የሚቀረፉባት ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ በሚደረገው ጉዞ ላይ ሌላ አንድ ትልቅ ምዕራፍና ስኬት ነው። አመካካሪዎች ይህን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በታማኝነት የሚሸከሙ ባለአደራዎች መሆናቸውን ጠቅሰውም፤ ራሳቸውን የሀገሪቱን ማህበራዊ፣ ሕዝባዊና ዴሞክራሲያዊ መጻኢ ዕድል በጋራ የሚገነቡ ታሪክ ሰሪዎች አድርገው ማየት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ይህ ሥልጠና አመካካሪዎች የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ክብር የሚጠብቁ እንዲሁም ለሰላም፣ ለፍትህና ለአንድነት ያላቸውን የጋራ ምኞት የሚያሳኩ ምክክሮችን መምራት የሚያስችላቸውን እውቀት፣ ክህሎትና እሴት መጨበጥ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ አመካካሪዎች በጉባኤው ወቅት ሁሉም ተሳታፊዎች እኩል የመናገርና የመሳተፍ ዕድል እንዳላቸው ማረጋገጥ፣ በውይይት ወቅት የሚነሱ አለመግባባቶችን በአግባቡ መምራት እንዲሁም ውይይቱ ወደ ጋራ መግባባት እንዲያመራ መንገድ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት፡፡ አመካካሪዎች ይህንን ትልቅ ሀገራዊ አደራ በትሕትና፣ በገለልተኝነት እና በትዕግሥት እንዲወጡትም አደራ ብለዋል።
ምርጫ ቦርድ የ723 የምርጫ ክልሎች ውጤት መጽደቁን ገለጸ
Jun 17, 2026 1384
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከተካሄደባቸው የምርጫ 1 ሺህ 139 የምርጫ ክልሎች መካከል የ723ቱ ውጤት መጽደቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ምርጫውን አስመልክቶ መግለጫ እየሰጠ ነው። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በመግለጫው ላይ እንዳሉት፤ በአጠቃላይ ካሉት 1ሺህ 139 የምርጫ ክልሎች መካከል የ723ቱ የምርጫ ክልሎች ውጤቶች በቦርዱ ፀድቀዋል። ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ አብዛኛዎቹ ቅሬታዎችም በህግ አካል ታይተው እልባት ማግኘታቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ተቋማትን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እየሠራች ነው - አምባሳደር ፀጋአብ ከበደ
Jun 17, 2026 675
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ተቋማትን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላምን ማስፈን የሚያስችሉ መዋቅራዊ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን በጄኔቫ የተመድ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ፀጋአብ ክበበው ገለጹ። 62ኛው የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ከሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው እየተካፈሉ የሚገኙት በጄኔቫ የተመድ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ፀጋአብ ክበበው የኢትዮጵያን ሀገራዊ መግለጫ (ሪፖርት) በስብሰባው ላይ አቅርበዋል። መንግሥት የዲሞክራሲ ተቋማትን ለማጠናከርና በሀገር በቀል ፍላጎት ላይ የተመሰረተውን የሪፎርም አጀንዳ ለማስቀጠል እያከናወናቸው ያሉትን ውጤታማ ተግባራትን አንስተዋል። አምባሳደሩ በቅርቡ የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተዓማኒና ሁሉን አካታች በሆነ መልኩ መካሄዱን ጠቅሰው ይህም የኢትዮጵያን ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ምኞትና ፍላጎት በተግባር ያሳየ መሆኑን አስገንዝበዋል። ምርጫው በስኬት መጠናቀቁ፣ የዲሞክራሲ ሥርዓቱን ለማጎልበትና ተቋማትን ለማጠናከር የተወሰደ ሌላው ትልቅ እርምጃ መሆኑንም ጠቅሰዋል። መንግሥት በሀገሪቱ አስተማማኝ ሰላምን ለማስፈንና በሀገር ባለቤትነት የሚመራውን የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ቀጣይነት ያለው ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አምባሳደር ፀጋአብ በሪፖርቱ ላይ አጽንኦት ሰጥተው አንስተዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደት አሁን ላይ የመጨረሻውና ወሳኙ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ጠቅሰው፤ በመጪው ሐምሌ ወር 2018 ዓ.ም የምክክር ጉባኤ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። ጉባኤው ሰፊ ሀገራዊ መግባባትን፣ ዕርቅ እና ዘላቂ ሰላምን ለመፍጠር ታሪካዊ ምዕራፍ እንደሚሆንም አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሪፖርት የሕግ የበላይነትን ይበልጥ ለማስከበር፣ የሲቪክ ምህዳሩን ለማስፋት እንዲሁም የሲቪል ማህበራት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና ባለድርሻ አካላት በዋና ዋና ሀገራዊ ሂደቶች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ እየተወሰዱ ያሉ መዋቅራዊ እርምጃዎችንም በስፋት አካቷል። ኢትዮጵያ መርህን ለተከተለ ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ ያላትን የጸና አቋምም አምባሳደሩ አንስተዋል። ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቢሮ (OHCHR) ጋር ውይይት፣ ትብብር፣ የጋራ መከባበር እና ብሔራዊ ባለቤትነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ገንቢ ትብብር ለመፍጠር ያላትን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል። በ62ኛው የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ አጀንዳዎች ላይ ኢትዮጵያ በንቃት እየተሳተፈች ትገኛለች። ኢትዮጵያ ለዜጎቿ ሁሉ የተመቸች ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊትና የበለጸገች ሀገር ለመገንባት የምታደርጋቸውን ጥረቶች አጠናክራ እንደምትቀጥልም በአጽንኦት አንስተዋል። የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለጹ
Jun 17, 2026 892
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቻይና የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ መስኮች ግንኙነታቸውን አጠናክረው ለመቀጠል እንደሚሰሩ አስታወቁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ጋር ዛሬ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ እያደገ በሚገኘው የኢትዮጵያ እና የቻይና ትብብርና የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። ሁለቱ ወገኖች በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች፣ በተለይም በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አስተዳደር፣ እንዲሁም በአረንጓዴ ልማት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዙ የቅድሚያ የትኩረት ጉዳዮች ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ የሚካሄደውን 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ 32) አስመልክቶ የሚደረጉ የሎጅስቲክስ ዝግጅቶችን መደገፍ በሚቻልበት የትብብር ሁኔታ ላይም መክረዋል። አምባሳደር ሃደራ አበራ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን አጋርነት ለማስቀጠል ያላትን አቋም እንደምታደንቅ ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ መስኮች ትብብራቸውን አጠናክረው ለመቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የንግዱ ማህበረሰብ በሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ባለቤት እና አሳላጭ መሆን ይጠበቅበታል
Jun 17, 2026 1079
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የንግዱ ማህበረሰብ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ንቁ ተሳታፊ፣ ባለቤት እና የሂደቱ አሳለጭ በመሆን ለስኬቱ የበኩሉን ሚና አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር በመተባበር "በሀገራዊ ምክክር ሂደት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ" በሚል መሪ ሀሳብ በሀገራዊ ሰላምና መረጋጋት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል። የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የግሉን ዘርፍ በመወከል ከመንግስት ጋር ምክክር የሚያደርግ ተቋም ነው። ኮሚሽነር አምባዬ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የብዝሀነት የዕምቅ አቅም ባለቤት ብትሆንም ለዘመናት ከግጭት አዙሪት መውጣት አቅቷት ቆይታለች። ስለሆነም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዜጎች ያልተግባቡባቸውን ዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች በምክክር መፍታት የሚችሉበትን አውድ መፍጠሩን ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲወያዩና ለችግሮች የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ የተቋቋመ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያውያን በነፃነት የሚነጋገሩበትን አውድ መፍጠር፣ የልዩነት መንስኤ የሆኑ አጀንዳዎችን መለየት እና በሂደቱ ላይ የሚወያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመለየት ብሎም ሌሎች ውጤታማ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ የምክክር ሂደቱ አካታችና ሁሉን አቀፍ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ነጋዴዎችና የንግድ ተቋማት ባለቤቶች ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ፌዴራል ድረስ በሂደቱ ላይ ንቁ ተሳታፊና አሳላጭ በመሆን ገንቢ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። የንግዱ ማህበረሰብ ለዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ከፍተኛ ሚና እንዳለው በመጥቀስ፣ በቀጣይ በዋናው የምክክር ጉባኤ ላይ የህዝቡን ተሳትፎ በማጎልበትና ባለቤትነት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤትም ይህንን ሚናውን እንዲወጣ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ዓይናለም አባይነህ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የጀመረው ሂደት ለኢትዮጵያ የንግዱ ማህበረሰብ ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ምህዳር ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል። የንግዱ ማህበረሰብ የግሉን ዘርፍ በመወከል ለምክክር ሂደቱ ስኬት የበኩሉን ሚና እንደሚወጣ ገልጸው፤ ምክክሮች ወደ ተጨባጭ ውጤቶች እንዲቀየሩ የበኩላቸውን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩም አረጋግጠዋል። ምክር ቤቱ ለኮሚሽኑ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚያደርግ በመጥቀስ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል፡፡
መገናኛ ብዙሃን በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ የከፈለውን ዋጋ ለዓለም አሳይተዋል - ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ
Jun 16, 2026 2374
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ህዝብ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያሳየውን ቁርጠኝነትና የከፈለውን ዋጋ ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ መገናኛ ብዙሃን የጎላ ሚና መጫወታቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ ገለጹ። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት "ኢትዮጵያ መርጣለች፣ ኢትዮጵያ አሸንፋለች" በሚል መሪ ሃሳብ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫን የሚመለከቱ መረጃዎችን ከመራጮች ምዝገባ እስከ ምርጫው ዕለት በተከታታይ ለህዝብ በማድረስ ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ልምምድ የላቀ ሙያዊ አስተዋጽኦ ላደረጉ መገናኛ ብዙሃን የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል። በሥነ-ስርዓቱ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ፣ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። ሚኒስትር እናትዓለም በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ እውነተኛና ትክክለኛ መረጃን በማስተጋባት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መቆም የመገናኛ ብዙሃን ተቀዳሚ ተግባር ነው። የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃኑ የሀገርን ዴሞክራሲ በሀገር ልጅ ድምፅ ለዓለም በማስተጋባት ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። ይህም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም እና ክብር የማስቀደም ጉዳይ በመሆኑ ለቀጣዩ ትውልድ የፀናች ኢትዮጵያን ለማስተላለፍ መሰረት መጣሉን አስገንዝበዋል። ለአብነትም መገናኛ ብዙሃን ህዝቡ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰለጠነ መንገድ በመምረጥ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሰጠውን ዋጋ በሚገባ ለዓለም ማሳየታቸውን አስረድተዋል። ከዚህ ባለፈም የፈጠራና የሀሰተኛ መረጃዎችን በማምከን የኢትዮጵያን ስኬት ለማይሹ ሃይሎች ትልቅ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ገልጸው፤ ለዚህም ኢትዮጵያ ታመሰግናችኋለች ብለዋል። በቀጣይም ለሀገር አንድነት ይበልጥ በመስራት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ገንቢ ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኢዜአ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ፤ ተቋሙ በዋናነት የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት በሚያስከብሩ ትክክለኛ መረጃዎች ላይ ተመስርቶ እየሰራ መሆኑን አመልክተው፤ ለጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ሚዲያዎች በሚባል ደረጃ ፈጣን፣ ትክክለኛ ወቅታዊ መረጃ እንዲያገኙ ማስቻሉን አብራርተዋል። የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ፤ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመገናኛ ብዙሃን በጋራና በትብብር በመሥራት የሀገሪቷን ታሪካዊ ጠላቶች ያሳፈሩበት እንደነበር ተናግረዋል። የኢቢኤስ (EBS) ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ነብዩ ጥዑመልሳን በበኩላቸው፤ በምርጫው ወቅት በመገናኛ ብዙሃን መካከል የታየውን ጠንካራ ቅንጅት አድንቀው፣ ይህም በጋራ ለሀገራዊ ዓላማ የመቆምን አስፈላጊነት ያሳየ ነው ብለዋል። የኦቢኤን ሥራ አስፈፃሚ ፍስሃ በላይነህ፣ሚዲያው ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ባህል ግንባታን ለማሳደግ በማሰብ የተለያዩ የክርክር መድረኮችን በ19 ቋንቋዎች ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። የአሚኮ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ሰጥዬ፤ መገናኛ ብዙሃን በቅንጅት መስራት ከቻሉ የሀገርን ክብር እና ጥቅም ማስጠበቅ እንደሚችሉ ያረጋገጡበት ነው ብለዋል። የአሃዱ ሬዲዮና ቴሌቪዥኝ ስራ አስፈጻሚ ጥበቡ በለጠ፤ ከሂደቱ እንደ ሚዲያ ተቋም ትልቅ ልምድ ማግኘታቸውንና ይህም በቀጣይ ሀገራዊ ጥቅምን የሚያስከብር ተግባራትን በብቃት ለመወጣት እንደሚያስችል ገልጸዋል።
ፖለቲካ
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው ለመስጠትና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት የሚጥሩ አካላትን መታገል የጋራ ሃላፊነታችን ነው - የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Jun 18, 2026 72
ሀዋሳ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው ለመስጠትና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት የሚጥሩ አካላትን መታገል የጋራ ሃላፊነታችን ነው ሲሉ በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በሲዳማ ክልል የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገር ብሄራዊ ጥቅም፣ ሰላምና ልማት ላይ ያላቸውን አቋምና ምልከታ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የሀገር ሰላምና ልማትን ማደናቀፍ፣ ከብሄራዊ ጥቅም በተቃራኒ መቆም በየትኛውም መመዘኛ ትክክል ያልሆነ ተግባር መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው ለመስጠትና የሕዝብን ሰላም ለማናጋት የሚጥሩ ባንዳዎችን መታገል የጋራ ሃላፊነታችን ነው ብለዋል። የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራሲ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ በለጠ ሲጌቦ፤ በሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ ሰላምና ልማት ላይ ያለልዩነት የምንሰራበት የጋራ አጀንዳችንና ሀገራዊ ግዴታችን ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ለዘላቂ ልማትና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ተቀራርበንና ተደጋግፈን ለመስራት ተዘጋጅተናል ነው ያሉት። በሀሳብ የበላይነት በሰላማዊ መንገድ መታገል የማይፈልጉ እንዲሁም በባንዳነት የተሰለፉ አካላት በየትኛውም መመዘኛ ታሪካዊ ስህተት እየፈፀሙ መሆኑን ሊገነዘቡ ይገባል ብለዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው ለመስጠትና ሰላምን ለማናጋት የሚጥሩ አካላትን መታገል የጋራ ሀገራዊ ሃላፊነታችን በመሆኑ በቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የጋራ ምክር ቤቱ ሥራ አስፈጻሚና በክልሉ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ተወካይ ወይዘሮ ሃረገወይን ዘሪሁን፤ የሰላምና የልማት ጉዳይ ለማንም የማይተው የሁላችንም ቋሚ አጀንዳ ነው ብለዋል። በመሆኑም የህዝብን ሰላምና ልማት በማደናቀፍ ሀገርን ለማፍረስ የሚጥሩ ጸረ ሰላም ሃይሎችን ድርጊት በመታገል በኢትዮጵያ ጠንካራ ሀገረ መንግስት የመገንባት ሃላፊነታችንን ለመወጣት እንሰራለን ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያ የብዝሃ እምነትና ባህል ሀገር መሆኗን አስታውሰው፣ ሁልጊዜም ልዩነቶችን በነባር ባህሎችና በምክክር በመፍታት ጠንካራ መንግስትና ሃገር መገንባት ይገባናል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለመጉዳትና ሰላሟን ለማናጋት የሚደረግ ጥረት ክህደት ስለመሆኑ አንስተው ከምንም በማስቀደም ለሀገር መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) ሊቀመንበር ለገሰ ላንቃሞ በበኩላቸው፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም፣ ሰላምና ልማት አጠናክሮ ማስቀጠል የፓርቲያችን የማይናወጥ አቋም ነው ብለዋል። የውጭ ባዳዎችንና የውስጥ ባንዳዎችን የጥፋት አጀንዳ ተቀብለው ልዩነቶችን በሃይል ለመፍታት እየተንቀሳቀሱ ያሉ ጸረ ሰላም ሃይሎችን እንደሚታገሉ ገልጸው፣ በሀገር ብሔራዊ ጥቅም ላይ ልዩነት የለንም ብለዋል። ለዘመናት ሳያግባቡን የቆዩ ሀገራዊ ጉዳዮችን ለመፍታት ታሪካዊ እድል የሰጠንን ሀገራዊ ምክክር በመጠቀም ችግሮችን በምክክር በዘላቂነት መፍታትና ሀገርን ማጽናት አለብን ሲሉም ገልጸዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቅቡልነት ያለው መንግሥትና ጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት መሠረት የጣለ ነው
Jun 18, 2026 88
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ቅቡልነት ያለው መንግሥትና ጠንካራ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት መሠረት የጣለ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን ገለጹ። ኢትዮጵያ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበትንና 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበትን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በስኬት አካሂዳለች። ዜጎች በየምርጫ ጣቢያቸው ከማለዳ 12 ሰዓት እስከ እኩለ ሌሊት በነቂስ በመውጣት ድምጻቸውን ሰጥተዋል፡፡ የምርጫ ሒደቱን በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን እንደገለጹት፥ ምርጫው የበርካታ ፓርቲዎች ፉክክር የታየበትና በሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁም በሀገሪቱ የሰከነ የፖለቲካ ባህል እየተገነባ መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ ዓይነቱ አካሄድ በቀጣይ ለሚመሰረተው መንግስት ጠንካራ ሕዝባዊ ቅቡልነት ከመስጠቱ በላይ፣ ለተረጋጋ የፖለቲካ ሂደትና ለልማት ዋነኛ መሠረት ይሆናል ብለዋል። በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ጌትዬ ትርፌ (ዶ/ር)፥ የምርጫ ሂደቱ ከዚህ በፊት ከተካሄዱ ምርጫዎች እጅግ የተሻለ ዴሞክራሲያዊነት የታየበት መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ህብረተሰቡ ሀገርን በማስቀደም ከቅድመ ምርጫው እስከ ድህረ ምርጫ ድረስ ያሳዩት ኃላፊነት የተሞላበት እንቅስቃሴ የሚደነቅ ነው ብለዋል። በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት መገናኛ ብዙኃን ያለምንም ልዩነት ሁሉንም የፖለቲካ ፓርቲዎች ለማሳተፍ የነበራቸው ቁርጠኝነትም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሕዝቡ የሰከነ እንቅስቃሴ ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማስቻሉንም በመግለጽ፡፡ በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የፖሊሲና ስትራቴጂ ተመራማሪ ተመስገን ዋለልኝ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዘንድሮው ምርጫ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጹን የሰጠበት፣ ለዴሞክራሲ ባህል መዳበር ያለውን ቁርጠኝነትም በጽናቱ ያረጋገጠበት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ መብቱን የመጠቀምና የመጠበቅ ብስለቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ያሳየ ምርጫ እንደሆነም አንስተዋል። በዚህ ምርጫ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ያለምንም ጫና የመወዳደር፣ ሀሳባቸውን በነጻነት የማንጸባረቅና አማራጭ ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የማቅረብ እድል ማግኘታቸውንም ጠቅሰዋል። ምርጫው በአሳታፊነቱ፣ በፍትሐዊነቱና በተፈጠሩ ምቹ የመወዳደሪያ ምህዳሮች በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ምዕራፍ ሽግግር የተደረገበት መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ህብረትና የኢጋድ የታዛቢዎች ልዑክ ቡድን ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ የታየበት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን ማረጋገጣቸውን መግለጻቸው ይታወቃል።
ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪዎች የግንዛቤና የክህሎት ሥልጠና መስጠት ተጀመረ
Jun 18, 2026 71
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪዎች ያዘጋጀው የግንዛቤና የክህሎት ሥልጠና መስጠት ጀምሯል። በአዲስ አበባ እየተሰጠ የሚገኘው ይህ የአመካካሪዎች ሥልጠና ከዛሬ ሰኔ 11 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሰባት ቀናት እንደሚቆይ ተመላክቷል። በሥልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ እንደገለጹት፤ ይህ የሥልጠና መርሃ ግብር ልዩነቶች በምክክር የሚፈቱበት፣ በግልጽነትና በመግባባት የሚቀረፉባት ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ በሚደረገው ጉዞ ላይ ሌላ አንድ ትልቅ ምዕራፍና ስኬት ነው። አመካካሪዎች ይህን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በታማኝነት የሚሸከሙ ባለአደራዎች መሆናቸውን ጠቅሰውም፤ ራሳቸውን የሀገሪቱን ማህበራዊ፣ ሕዝባዊና ዴሞክራሲያዊ መጻኢ ዕድል በጋራ የሚገነቡ ታሪክ ሰሪዎች አድርገው ማየት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ይህ ሥልጠና አመካካሪዎች የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ክብር የሚጠብቁ እንዲሁም ለሰላም፣ ለፍትህና ለአንድነት ያላቸውን የጋራ ምኞት የሚያሳኩ ምክክሮችን መምራት የሚያስችላቸውን እውቀት፣ ክህሎትና እሴት መጨበጥ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ አመካካሪዎች በጉባኤው ወቅት ሁሉም ተሳታፊዎች እኩል የመናገርና የመሳተፍ ዕድል እንዳላቸው ማረጋገጥ፣ በውይይት ወቅት የሚነሱ አለመግባባቶችን በአግባቡ መምራት እንዲሁም ውይይቱ ወደ ጋራ መግባባት እንዲያመራ መንገድ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት፡፡ አመካካሪዎች ይህንን ትልቅ ሀገራዊ አደራ በትሕትና፣ በገለልተኝነት እና በትዕግሥት እንዲወጡትም አደራ ብለዋል።
ምርጫ ቦርድ የ723 የምርጫ ክልሎች ውጤት መጽደቁን ገለጸ
Jun 17, 2026 1384
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከተካሄደባቸው የምርጫ 1 ሺህ 139 የምርጫ ክልሎች መካከል የ723ቱ ውጤት መጽደቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ምርጫውን አስመልክቶ መግለጫ እየሰጠ ነው። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በመግለጫው ላይ እንዳሉት፤ በአጠቃላይ ካሉት 1ሺህ 139 የምርጫ ክልሎች መካከል የ723ቱ የምርጫ ክልሎች ውጤቶች በቦርዱ ፀድቀዋል። ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ አብዛኛዎቹ ቅሬታዎችም በህግ አካል ታይተው እልባት ማግኘታቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ተቋማትን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እየሠራች ነው - አምባሳደር ፀጋአብ ከበደ
Jun 17, 2026 675
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ተቋማትን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላምን ማስፈን የሚያስችሉ መዋቅራዊ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን በጄኔቫ የተመድ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ፀጋአብ ክበበው ገለጹ። 62ኛው የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ከሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው እየተካፈሉ የሚገኙት በጄኔቫ የተመድ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ፀጋአብ ክበበው የኢትዮጵያን ሀገራዊ መግለጫ (ሪፖርት) በስብሰባው ላይ አቅርበዋል። መንግሥት የዲሞክራሲ ተቋማትን ለማጠናከርና በሀገር በቀል ፍላጎት ላይ የተመሰረተውን የሪፎርም አጀንዳ ለማስቀጠል እያከናወናቸው ያሉትን ውጤታማ ተግባራትን አንስተዋል። አምባሳደሩ በቅርቡ የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተዓማኒና ሁሉን አካታች በሆነ መልኩ መካሄዱን ጠቅሰው ይህም የኢትዮጵያን ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ምኞትና ፍላጎት በተግባር ያሳየ መሆኑን አስገንዝበዋል። ምርጫው በስኬት መጠናቀቁ፣ የዲሞክራሲ ሥርዓቱን ለማጎልበትና ተቋማትን ለማጠናከር የተወሰደ ሌላው ትልቅ እርምጃ መሆኑንም ጠቅሰዋል። መንግሥት በሀገሪቱ አስተማማኝ ሰላምን ለማስፈንና በሀገር ባለቤትነት የሚመራውን የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ቀጣይነት ያለው ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አምባሳደር ፀጋአብ በሪፖርቱ ላይ አጽንኦት ሰጥተው አንስተዋል። የሀገራዊ ምክክር ሂደት አሁን ላይ የመጨረሻውና ወሳኙ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ጠቅሰው፤ በመጪው ሐምሌ ወር 2018 ዓ.ም የምክክር ጉባኤ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። ጉባኤው ሰፊ ሀገራዊ መግባባትን፣ ዕርቅ እና ዘላቂ ሰላምን ለመፍጠር ታሪካዊ ምዕራፍ እንደሚሆንም አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ሪፖርት የሕግ የበላይነትን ይበልጥ ለማስከበር፣ የሲቪክ ምህዳሩን ለማስፋት እንዲሁም የሲቪል ማህበራት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና ባለድርሻ አካላት በዋና ዋና ሀገራዊ ሂደቶች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ እየተወሰዱ ያሉ መዋቅራዊ እርምጃዎችንም በስፋት አካቷል። ኢትዮጵያ መርህን ለተከተለ ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ ያላትን የጸና አቋምም አምባሳደሩ አንስተዋል። ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቢሮ (OHCHR) ጋር ውይይት፣ ትብብር፣ የጋራ መከባበር እና ብሔራዊ ባለቤትነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ገንቢ ትብብር ለመፍጠር ያላትን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል። በ62ኛው የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ አጀንዳዎች ላይ ኢትዮጵያ በንቃት እየተሳተፈች ትገኛለች። ኢትዮጵያ ለዜጎቿ ሁሉ የተመቸች ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊትና የበለጸገች ሀገር ለመገንባት የምታደርጋቸውን ጥረቶች አጠናክራ እንደምትቀጥልም በአጽንኦት አንስተዋል። የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለጹ
Jun 17, 2026 892
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቻይና የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ መስኮች ግንኙነታቸውን አጠናክረው ለመቀጠል እንደሚሰሩ አስታወቁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ጋር ዛሬ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ እያደገ በሚገኘው የኢትዮጵያ እና የቻይና ትብብርና የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። ሁለቱ ወገኖች በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች፣ በተለይም በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አስተዳደር፣ እንዲሁም በአረንጓዴ ልማት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዙ የቅድሚያ የትኩረት ጉዳዮች ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ የሚካሄደውን 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ 32) አስመልክቶ የሚደረጉ የሎጅስቲክስ ዝግጅቶችን መደገፍ በሚቻልበት የትብብር ሁኔታ ላይም መክረዋል። አምባሳደር ሃደራ አበራ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን አጋርነት ለማስቀጠል ያላትን አቋም እንደምታደንቅ ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ መስኮች ትብብራቸውን አጠናክረው ለመቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የንግዱ ማህበረሰብ በሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ባለቤት እና አሳላጭ መሆን ይጠበቅበታል
Jun 17, 2026 1079
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የንግዱ ማህበረሰብ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ንቁ ተሳታፊ፣ ባለቤት እና የሂደቱ አሳለጭ በመሆን ለስኬቱ የበኩሉን ሚና አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር በመተባበር "በሀገራዊ ምክክር ሂደት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ" በሚል መሪ ሀሳብ በሀገራዊ ሰላምና መረጋጋት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል። የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የግሉን ዘርፍ በመወከል ከመንግስት ጋር ምክክር የሚያደርግ ተቋም ነው። ኮሚሽነር አምባዬ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የብዝሀነት የዕምቅ አቅም ባለቤት ብትሆንም ለዘመናት ከግጭት አዙሪት መውጣት አቅቷት ቆይታለች። ስለሆነም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዜጎች ያልተግባቡባቸውን ዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች በምክክር መፍታት የሚችሉበትን አውድ መፍጠሩን ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲወያዩና ለችግሮች የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ የተቋቋመ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያውያን በነፃነት የሚነጋገሩበትን አውድ መፍጠር፣ የልዩነት መንስኤ የሆኑ አጀንዳዎችን መለየት እና በሂደቱ ላይ የሚወያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመለየት ብሎም ሌሎች ውጤታማ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ የምክክር ሂደቱ አካታችና ሁሉን አቀፍ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ነጋዴዎችና የንግድ ተቋማት ባለቤቶች ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ፌዴራል ድረስ በሂደቱ ላይ ንቁ ተሳታፊና አሳላጭ በመሆን ገንቢ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። የንግዱ ማህበረሰብ ለዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ከፍተኛ ሚና እንዳለው በመጥቀስ፣ በቀጣይ በዋናው የምክክር ጉባኤ ላይ የህዝቡን ተሳትፎ በማጎልበትና ባለቤትነት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤትም ይህንን ሚናውን እንዲወጣ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ዓይናለም አባይነህ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የጀመረው ሂደት ለኢትዮጵያ የንግዱ ማህበረሰብ ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ምህዳር ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል። የንግዱ ማህበረሰብ የግሉን ዘርፍ በመወከል ለምክክር ሂደቱ ስኬት የበኩሉን ሚና እንደሚወጣ ገልጸው፤ ምክክሮች ወደ ተጨባጭ ውጤቶች እንዲቀየሩ የበኩላቸውን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩም አረጋግጠዋል። ምክር ቤቱ ለኮሚሽኑ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚያደርግ በመጥቀስ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል፡፡
መገናኛ ብዙሃን በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ የከፈለውን ዋጋ ለዓለም አሳይተዋል - ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ
Jun 16, 2026 2374
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ ህዝብ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያሳየውን ቁርጠኝነትና የከፈለውን ዋጋ ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ መገናኛ ብዙሃን የጎላ ሚና መጫወታቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ ገለጹ። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት "ኢትዮጵያ መርጣለች፣ ኢትዮጵያ አሸንፋለች" በሚል መሪ ሃሳብ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫን የሚመለከቱ መረጃዎችን ከመራጮች ምዝገባ እስከ ምርጫው ዕለት በተከታታይ ለህዝብ በማድረስ ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ልምምድ የላቀ ሙያዊ አስተዋጽኦ ላደረጉ መገናኛ ብዙሃን የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል። በሥነ-ስርዓቱ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ፣ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። ሚኒስትር እናትዓለም በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ እውነተኛና ትክክለኛ መረጃን በማስተጋባት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መቆም የመገናኛ ብዙሃን ተቀዳሚ ተግባር ነው። የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃኑ የሀገርን ዴሞክራሲ በሀገር ልጅ ድምፅ ለዓለም በማስተጋባት ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። ይህም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም እና ክብር የማስቀደም ጉዳይ በመሆኑ ለቀጣዩ ትውልድ የፀናች ኢትዮጵያን ለማስተላለፍ መሰረት መጣሉን አስገንዝበዋል። ለአብነትም መገናኛ ብዙሃን ህዝቡ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰለጠነ መንገድ በመምረጥ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሰጠውን ዋጋ በሚገባ ለዓለም ማሳየታቸውን አስረድተዋል። ከዚህ ባለፈም የፈጠራና የሀሰተኛ መረጃዎችን በማምከን የኢትዮጵያን ስኬት ለማይሹ ሃይሎች ትልቅ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ገልጸው፤ ለዚህም ኢትዮጵያ ታመሰግናችኋለች ብለዋል። በቀጣይም ለሀገር አንድነት ይበልጥ በመስራት ለጠንካራ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ገንቢ ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኢዜአ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ፤ ተቋሙ በዋናነት የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት በሚያስከብሩ ትክክለኛ መረጃዎች ላይ ተመስርቶ እየሰራ መሆኑን አመልክተው፤ ለጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ሚዲያዎች በሚባል ደረጃ ፈጣን፣ ትክክለኛ ወቅታዊ መረጃ እንዲያገኙ ማስቻሉን አብራርተዋል። የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ፤ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመገናኛ ብዙሃን በጋራና በትብብር በመሥራት የሀገሪቷን ታሪካዊ ጠላቶች ያሳፈሩበት እንደነበር ተናግረዋል። የኢቢኤስ (EBS) ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ነብዩ ጥዑመልሳን በበኩላቸው፤ በምርጫው ወቅት በመገናኛ ብዙሃን መካከል የታየውን ጠንካራ ቅንጅት አድንቀው፣ ይህም በጋራ ለሀገራዊ ዓላማ የመቆምን አስፈላጊነት ያሳየ ነው ብለዋል። የኦቢኤን ሥራ አስፈፃሚ ፍስሃ በላይነህ፣ሚዲያው ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ባህል ግንባታን ለማሳደግ በማሰብ የተለያዩ የክርክር መድረኮችን በ19 ቋንቋዎች ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። የአሚኮ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ሰጥዬ፤ መገናኛ ብዙሃን በቅንጅት መስራት ከቻሉ የሀገርን ክብር እና ጥቅም ማስጠበቅ እንደሚችሉ ያረጋገጡበት ነው ብለዋል። የአሃዱ ሬዲዮና ቴሌቪዥኝ ስራ አስፈጻሚ ጥበቡ በለጠ፤ ከሂደቱ እንደ ሚዲያ ተቋም ትልቅ ልምድ ማግኘታቸውንና ይህም በቀጣይ ሀገራዊ ጥቅምን የሚያስከብር ተግባራትን በብቃት ለመወጣት እንደሚያስችል ገልጸዋል።
ማህበራዊ
በሲዳማ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው
Jun 18, 2026 7
ሀዋሳ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል 49 ሺህ ተማሪዎች የስምንተኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና እየወሰዱ ነው። የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ በየነ በራሳ በሀዋሳ ከተማ ሐይቅ ዳር አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ክልላዊ ፈተናውን አስጀምረዋል፡፡ አቶ በየነ በዚህ ወቅት እንደገለጹት የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለፈተናው ለማዘጋጀት ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ለፈተናው አስፈላጊው ዘግጅት ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው፣ በዛሬው እለትም 49 ሺህ ተማሪዎች ፈተናውን በ232 ልዩ የፈተና ማዕከላት እየወሰዱ መሆኑን ገልጸዋል። ፈተናው በልዩ ማዕከላት መሰጠቱ ጤናማ የፈተና ሂደት እንዲኖር፣ ኩረጃን ለማስቀረት እና ተገቢ ክትትልና ቁጥጥር ለማድረግ ጠቀሜታ እንዳለውም ተናግረዋል።
በክልሉ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት እየተመዘገበባቸው ነው - ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ
Jun 18, 2026 16
ሐረር፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት እየተመዘገበባቸው መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ። በሐረሪ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መሰጠት ተጀምሯል። የሐረሪ ክልል በአዲሱ የፈተና ሥርዓት የተማሪዎችን የማሳለፍ ምጣኔ እና አጠቃላይ የውጤት ጥራት ለማሳደግ ልዩ ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርቶችንና የክለሳ ፕሮግራሞችን ሲተገብር ቆይቷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተሰጠ የሚገኘውን የ8ኛ ክፍል ፈተና ዛሬ ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት በክልሉ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል። በተከናወኑ ተግባራትም የተሻሉ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸው፤ በክልሉ እየታየ የሚገኘው የትምህርት ተሳትፎ፣ ጥራትና የተማሪ ውጤት የማጎልበት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ነገዎ በበኩላቸው ለፈተናው አስፈላጊው ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል ብለዋል። በክልሉ በአጠቃላይ በገጠርና በከተማ 30 የፈተና ጣቢያዎች የተዘጋጁ ሲሆን 4ሺህ 614 ተማሪዎች ፈተናውን እየወሰዱ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ትምህርት ቢሮው ተማሪዎችን ለፈተና ለማብቃትና ውጤትን ለማሻሻል በትኩረት ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል፡፡ በተለይም ተማሪዎችን ለፈተና ለማብቃት በትምህርት ቤቶች የማጠናከሪያ ትምህርትና ሞዴል ፈተና አዘጋጅቶ የመስጠትና ሌሎች ተግባራት ሲከናወኑ መቆታቸውን አስታውሰዋል፡፡
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተማሪዎች ተከታታይነት ያለው የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ውጤታማ እንዲሆኑ ተሰርቷል
Jun 18, 2026 18
አሶሳ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተማሪዎች ተከታታይነት ያለው የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ውጤታማ እንዲሆኑ መሠራቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መሰጠት መጀመሩን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል። በሀገሪቱ የተጀመረውን የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ሪፎርም ተከትሎ፣ የብሔራዊና የክልላዊ ፈተናዎች አሰጣጥ ሥርዓት ጥብቅና ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን መደረጉ ይታወሳል። ይህንን አዲስ የፈተና ሥርዓት ተማሪዎች በብቃት መወጣት እንዲችሉ፣ መደበኛውን የመማር-ማስተማር ሂደት ከማጠናከር ባለፈ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ ከትምህርት ሰዓታት ውጭ ተከታታይነት ያላቸው የክለሳና የማጠናከሪያ ፕሮግራሞችን መስጠት የክልሎች ዋነኛ ስትራቴጂ ሆኖ እየተገበረ ይገኛል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮም ካለፉት ዓመታት ጀምሮ ፍትሐዊና ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ለማድረስ በርካታ ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ተገልጿል። በተለይም ተማሪዎች በተለያዩ ማኅበራዊና አካባቢያዊ ምክንያቶች ሊያመልጧቸው የሚችሉ ትምህርቶችን ለማካካስና በተለይም የ6ኛ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን ውጤታማነት ለማሳደግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሠራ መቆየቱን ገልጿል። የቢሮው የስርዓተ ትምህርት እና ተቋማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ሙሐመድ ኡስማን ዛሬ በአቡራሞ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ፈተናውን ሲያስጀምሩ እንዳሉት፤ ተማሪዎች ተከታታይነት ያለው የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ውጤታማ እንዲሆኑ ተሰርቷል። በተለይም ቢሮው በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለፈተናው ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ጠቅሰው፥ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ሰፋፊ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል። ተማሪዎች ፈተናውን በተረጋጋ ሁኔታ እንዲፈተኑ አስፈላጊውን የስነ ልቦና እና ምክር እንደተሰጣቸውም ተናግረዋል። በዘንድሮው ዓመት በክልሉ በ313 ትምህርት ቤቶች ላይ ከ21 ሺህ በላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና እየወሰዱ ይገኛሉ ብለዋል። በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል የፈተና የእርማት ማሽን ግዢ በመፈጸሙ የፈተናውን ውጤት በአጭር ጊዜ ውስጥ በማሳወቅ ተማሪዎች ለቀጣይ የትምህርት ጊዜ ዝግጁ እንዲሆኑ ይደረጋል ነው ያሉት።
ተማሪዎችን ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ ማብቃት የተሻለ ትውልድ ለመገንባት ያግዛል
Jun 18, 2026 42
ጅግጅጋ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ ተማሪዎችን ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ በተሻለ የትምህርት ጥራት ማብቃት ሀገር ገንቢ ትውልድ ለመገንባት ያግዛል ሲሉ የሶማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ጉሌድ አህመድ አሊ ገለጹ። በሶማሌ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መሰጠት ተጀምሯል። በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ብቁ ዜጋ ለማፍራት ሰፊ የሪፎርም ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በተለይም የታችኛው የትምህርት እርከን ለተማሪዎች ቀጣይ የዕውቀት አድማስና ለተተኪው ትውልድ ሰብዕና ግንባታ ወሳኝ መሠረት በመሆኑ፣ አጠቃላይ የትምህርት ጥራቱ ትኩረት ተሰጥቶት ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከሚከናወኑ ቁልፍ ተግባራት መካከል ደግሞ ተማሪዎች በራስ መተማመናቸውን አሳድገው፣ ፈተናን በራሳቸው አቅም በመስራት የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ማስቻል ዋነኛው ነው። ዛሬ በተጀመረው የሶማሌ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናም ተማሪዎች በራሳቸው በመተማመን የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ መሰራቱ ነው የተገለጸው። ፈተናውን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢብራሂም ዑስማን እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ መሀመድ ሼክ አደን በሼክ አብዱሰላም 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው በይፋ አስጀምረዋል። የሶማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ጉሌድ አህመድ አሊ በወቅቱ እንዳሉት፤ ተማሪዎችን ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ በተሻለ የትምህርት ጥራት ማብቃት ሀገር ገንቢ ትውልድ ለመገንባት ያግዛል። ዛሬ በተጀመረው ክልል አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተናን 29 ሺህ 631 ተማሪዎች እንደሚወስዱ ገልጸው፤ ፈተናው በክልሉ 704 ትምህርት ቤቶችና በ113 የፈተና ጣቢያዎች እየተሠጠ ነው ብለዋል። የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናው ከሰኔ 11 ጀምሮ እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚሰጥም እንዲሁ።
ኢኮኖሚ
የኮሪደር ልማቱ የድሬዳዋን የተደበቀ ውበት በመግለጽ ከተማዋን ተመራጭ የስራና የመኖሪያ ማዕከል አድርጓታል
Jun 18, 2026 95
ድሬዳዋ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኮሪደር ልማቱ ታሪካዊ ቅርሶችን በጠበቀ መልኩ መከናወኑ ድሬዳዋን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪስት መዳረሻ እያደረጋት መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ አመራሮችና ነዋሪዎች ገለጹ። በድሬዳዋ ከተማ የሚገኙ ጥንታዊ ህንጻዎች፣ ልዩ የሥነ-ህንጻ ጥበብ እና የህዝቦቿ የባህል ብዝሃነት የቱሪስት መስህብ ሆነው መቆየታቸው ይታወቃል። በአሁኑ ወቅት በመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት፣ የከተማዋን ገጽታ በማዘመን፣ መንገዶቿን በማስፋትና ለነዋሪዎች ምቹ አካባቢን በመፍጠር ከፍተኛ ለውጥ እያመጣ ነው። የኮሪደር ልማቱ የድሬዳዋን ታሪካዊ ማንነት ጠብቆ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ዘርፍ አዲስ መነቃቃትን እየፈጠረ መሆኑን የአካባቢው አመራሮችና ነዋሪዎች ገልጸዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር በፕሮጀክት ፅህፈት ቤት የኮሪደር ልማት አስተባባሪ ወንድወሰን ጀንበሬ እንደተናገሩት፤ በአምስት አቅጣጫዎች የተከናወነው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገፅታና ውበት አጉልቶ አውጥቷል። በተለይም የከተማዋን ታሪካዊ ቅርሶችና ሃብቶች በጠበቀ መልኩ መከናወኑ ከተማዋን ዘመናዊ የኑሮና የስራ ተመራጭ ማዕከል እያደረጋት መሆኑን ጠቅሰዋል። በኮሪደር ልማቱ የተካተቱት ዘመናዊ መንገዶች፤ የመዝናኛ ማዕከላትና ሌሎች መሠረተ ልማቶች ድሬዳዋን ይበልጥ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እያደረጋት ይገኛልም ብለዋል። የአስተዳደሩ ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ነኢማ ኢብራሂም በበኩላቸው፤ የኮሪደር ልማቱ የቱሪዝም መዳረሻ የሆኑትን ሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ ሃብቶች ይበልጥ ማጉላቱን ገልጸዋል። በተለይም ለድሬዳዋ ከተማነት መሠረት በጣለውና የቱሪስት መዳረሻነት እያገለገለ በሚገኘው ታሪካዊ የባቡር ጣቢያ ጋር ተዋህዶ የተሰራው ልማት ቅርሱን ቱሪስቶች ይበልጥ እንዲጎበኙት እያደረገ ይገኛል ነው ያሉት። ከቱሪዝም መዳረሻዎች ባሻገር የነዋሪውን ትስስርና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዲጠናከር ምቹ መደላድል መፍጠሩን በመጠቆም። ሌላው አስተያየት ሰጭ ሼህ አብዶ ኡመር፤ የኮሪደር ልማቱ የተደበቀውን የድሬዳዋን ውበትና ገፅታ በመግለጽ ነዋሪውን ያስደሰተ መሠረታዊ ስራ መሆኑን ተናግረዋል። የኮሪደር ልማቱ የድሬዳዋን የአስፋልት፣ የእግረኛ እና የብስክሌት መንገዶችን ማስፋቱ የትራፊክ መጨናነቅና አደጋን በመቀነስ በኩል መሠረታዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ያሉት ደግሞ ሌላው ነዋሪ አቶ ሀብታሙ አሰፋ ናቸው። በተለይም የተፈጠሩት የመዝናኛና የአረንጓዴ ቦታዎች ለአረጋውያንና ለልጆች መዝናኛ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጠና ማህበራዊ መስተጋብርን እንደሚያዳብር አንስተዋል። የከተማ አስተዳደሩ እያከናወናቸው ካሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች በተጓዳኝ የግል ተቋማትም ከተማዋን በማደስና በማስዋብ በኩል ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ ወጪ ማድረጋቸውን ከአስተዳደሩ የፕሮጀክት እና የኮሪደር ልማት ፅህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን በማስፋፋት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው
Jun 18, 2026 89
ጊምቢ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ከቡና ልማት ጎን ለጎን የፍራፍሬ ልማትን በማስፋፋት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። በዞኑ በበጀት ዓመቱ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት መሰብሰቡም ተመላክቷል። በጽሕፈት ቤቱ የፍራፍሬ ልማት ባለሙያ ጂብሪል መንጌ እንዳስታወቁት፤ ዞኑ በስፋት ከሚታወቅበት የቡና ልማት ጎን ለጎን በፍራፍሬ ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ተግባራዊ የተደረገው የፍራፍሬ ልማትም የአርሶ አደሩን የሥራ ባህል በመቀየር በኩል አበረታች ውጤት ማስገኘቱን ተናግረዋል። ልማቱ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የምግብ ሥርዓትን ከማሻሻል አንጻር የላቀ ሚና እንዳለው ጠቁመው፤ ይህንን ታሳቢ ያደረገ እንቅስቃሴ በየደረጃው ሲካሄድ መቆየቱን አውስተዋል። በአሁኑ ወቅት 41 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት የፍራፍሬ ምርት መስጠት በሚችልበት ደረጃ ላይ የደረሰ ሲሆን፣ ከዚህም 2 ሚሊየን 399 ሺህ 710 ኩንታል የፍራፍሬ ምርት ተሰብስቦ ለገበያ ቀርቧል ብለዋል። ለገበያ ከቀረቡት የፍራፍሬ ምርቶች መካከል አናናስ፣ ሙዝ፣ ማንጎ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያና ብርቱካን ዋና ዋናዎቹ መሆናቸውን ገልጸው፤ የተሻሻለ የአቮካዶ ዝርያ ምርት ለውጭ ገበያ የሚቀርብ በመሆኑ፣ የአካባቢው አርሶ አደሮች ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱንም ተናግረዋል። በዚህ ዓመትም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ፤ ልማቱን ከአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ጋር በማቀናጀት የፍራፍሬ ችግኞችን በብዛትና በጥራት ለተከላ እየተዘጋጀ መሆኑን። የልማቱ ተሳታፊ የሆኑት የላሎ አሳቢ ወረዳ አርሶ አደር ታረቀ ጂሬኛ፤ ከዚህ ቀደም ሕይወታቸውንና ገቢያቸውን በቡና ልማት ላይ ብቻ መስርተው እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም መንግሥት ያመቻቸላቸውን የፍራፍሬ ችግኝና ምርጥ ዘር በመጠቀም በዘርፉ መሰማራታቸውንና ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በይዞታቸው ላይ ሙዝ፣ አቮካዶ እና አናናስ በማልማት በዓመት የተሻለ ገቢ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላው የሆማ ወረዳ አርሶ አደር ገረመው ጂሩ በበኩላቸው፤ ከግብርና ምርምር ማዕከል የወጣ የተሻሻለ የሙዝ ዝርያን በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል። ምርቱን ለአካባቢው ገበያ በማቅረብ በአንድ ዙር እስከ 30 ሺህ ብር ገቢ እያገኙ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይም ልማቱን በማጠናከር አቮካዶና ሙዝ በስፋት ለማልማት ማቀዳቸውን አስታውቀዋል።
የንግድ ምክር ቤቶችና ማህበራት ለህዝብ ያላቸውን ተደራሽነት በመጠቀም ለምክክሩ አሳታፊነትና አካታችነት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው
Jun 17, 2026 755
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018(ኢዜአ)፦ የንግድ ምክር ቤቶችና ማህበራት ለህዝብ ያላቸውን ተደራሽነት በመጠቀም ለሀገራዊ ምክክሩ አካታችነትና አሳታፊነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር በመተባበር "በሀገራዊ ምክክር ሂደት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ" በሚል መሪ ሀሳብ በሀገራዊ ሰላምና መረጋጋት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል፡፡ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የግሉን ዘርፍ በመወከል ከመንግሥት ጋር ምክክር የሚያደርግ ተቋም ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የብዝሀነትና የዕምቅ አቅም ባለቤት ብትሆንም ለዘመናት ከግጭት አዙሪት መውጣት አቅቷት ቆይታለች። ስለሆነም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዜጎች ያልተግባቡባቸውን ዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች በምክክር መፍታት የሚችሉበትን አውድ መፍጠሩን ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲወያዩና ለችግሮች የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ የተቋቋመ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያውያን በነፃነት የሚነጋገሩበትን አውድ መፍጠር፣ የልዩነት መንስኤ የሆኑ አጀንዳዎችን መለየት እና በሂደቱ ላይ የሚወያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመለየት ውጤታማ ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል፡፡ የምክክር ሂደቱ ከጅምሩ አካታችና ሁሉን አቀፍ መሆኑን ገልጸው፤ ነጋዴዎችና የንግድ ተቋማት ባለቤቶች ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ፌዴራል ድረስ በንቃት በመሳተፍ ሂደቱን ሲያሳልጡ ቆይተዋል ብለዋል፡፡ የንግድ ምክር ቤቶችና የንግዱ ማህበረሰብ ከተሳታፊነት ባለፈ በባለቤትነት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ተናግረዋል፡፡ የንግድ ምክር ቤቶችና ማህበራት ለህዝብ ያላቸውን ተደራሽነት በመጠቀም ለሀገራዊ ምክክሩ አካታችነትና አሳታፊነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ነው የገለጹት፡፡ የንግዱ ማህበረሰብ የሰላምን፣ የመቻቻል፣ የመግባባትና የአንድነት ትርክት በመፍጠር አምባሳደር መሆን ይችላል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ከህዝብ ጋር ባላቸው ቀረቤታ ተግባራዊ ድጋፍ ማድረግ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡ የንግዱ ማህበረሰብ ለዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ከፍተኛ ሚና እንዳለው በመጥቀስ፣ በቀጣይ በዋናው የምክክር ጉባኤ ላይ የህዝቡን ተሳትፎ በማጎልበትና የባለቤትነት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ዓይናለም አባይነህ (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ አስተማማኝ ሰላም ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የጀመረው ሂደት በኢትዮጵያ ለንግዱ ማህበረሰብ ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ምህዳር መፍጠር እንደሚያስችልም ገልጸዋል፡፡ የንግዱ ማህበረሰብ የግሉን ዘርፍ በመወከል ለምክክር ሂደቱ ስኬት የበኩሉን ሚና እንደሚወጣ ገልጸው፤ ምክክሮች ወደ ተጨባጭ ውጤቶች እንዲቀየሩ የበኩላቸውን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩም አረጋግጠዋል። የምክክር ኮሚሽኑ የጀመረው የምክክር ሂደት የጋራ እይታና የጋራ ልማት የሚያመጣ በመሆኑ ይህንኑ ጥረት በመደገፍ በንቃት እንደሚሳተፉ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት እና የአማራ ክልል ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤቶች የቦርድ አባል እስማኤል አሊ፤ ችግሮችና አለመግባባቶች በውይይት ቢፈቱ የመጀመሪያው ተጠቃሚ የንግዱ ማህበረሰብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እንደ ንግድ ማህበረሰብ ከቀበሌ ጀምሮ አጀንዳዎቻቸውን እያስያዙ በንቃት ሲሳተፉ እንደነበር ገልጸው፤ መወያየትና መመካከር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቦጋለ ቢታኒ በበኩላቸው፤ የምክክር ሂደቱ በሰፊው የተሳተፉበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የምክክር ኮሚሽኑ ሥራዎች የላቁ መሆናቸውን ገልጸው፤ የሰላሙ ባለቤት የሆነው የንግዱ ማህበረሰብ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነው ብለዋል፡፡
የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ረቂቅ አዋጅ ታሳቢ ያደረገው የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባሻገር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ነው
Jun 17, 2026 399
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018(ኢዜአ)፦የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ረቂቅ አዋጅ ታሳቢ ያደረገው የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባሻገር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ነው ሲል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ረቂቅ አዋጅ ላይ የሕዝብ እና የባለድርሻ አካላት ይፋዊ የውይይት መድረክ አካሂዷል። የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ላሌ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እድገት፣ የኢንዱስትሪ ልማት እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዋነኛ መሠረት ነው። ስለሆነም ኋላቀር ከሆነው የግብርና አሠራር በማላቀቅ ወደ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪ እና ገበያ መር ሥርዓት ማሻገር እንደሚገባ ገልጸዋል። ይህ ረቂቅ አዋጅ ሲጸድቅ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች እና ከፊል አርሶ አደሮችን በኩባንያ በማደራጀት የመጠቀም መብታቸውን የሚያረጋግጥ ይሆናል ብለዋል። እንዲሁም የእንስሳት ሀብታቸውን እና ጉልበታቸውን ወደ ካፒታል በመለወጥ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ የሚያስችል እንደሆነም ገልጸዋል። የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት፤ የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ማረጋገጥ የመንግሥት ዋና ትኩረት በመሆኑ ለዚህም በርካታ የፖሊሲ፣ የፕሮግራም እና የተቋም ሪፎርም ሥራዎች በሀገር ደረጃ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። ይህ ረቂቅ አዋጅ ግብርናን ለማሸጋገር ከሚከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች መካከል ዋነኛው ሲሆን፤ አርሶ አደሩና አርብቶ አደሩ የሀገር ውስጥ ኩባንያዎችን እና ካምፓኒዎችን እንዲመሰርቱ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡ አርብቶ አደሩን በማደራጀት፣ የእንስሳት ዝርያዎችን በማሻሻል እና የጤና አጠባበቅን በማዘመን፣ አርብቶ አደሩ የራንች ባለቤት እንዲሆንና ሥራዎቹን በባለቤትነት እንዲያከናውን ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ ረቂቅ አዋጅ እንደሆነ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ማንደፍሮ ንጉሤ እንደተናገሩት፤ ረቂቅ አዋጁ አርሶ አደሩን ወደ ኩባንያ አደረጃጀት በማሸጋገር የኢኮኖሚ እድገትን ይበልጥ ሊያፋጥኑ የሚችሉ አዳዲስ አቅሞችን መፍጠር ያስችላል ብለዋል። ሂደቱ አርሶ አደሮች ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን በምጣኔ ሀብት ከመደገፍ ባለፈ፤ በሀገሪቷ የኢኮኖሚ መዋቅር ውስጥ ግንባር ቀደም ተዋናይ እንዲሆኑ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። በመጪዎቹ አምስት እና አስር ዓመታት ውስጥ አርሶ አደሮቹን ወደ ከፍተኛ ደረጃ በማሸጋገር ድንበር ተሻጋሪ የንግድ ሥራዎችን የሚያከናውኑና በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሆኑ ትላልቅ የወጪ ንግድ ነጋዴዎች ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። በውይይቱ የተሳተፉት ባለድርሻ አካላት ረቂቅ አዋጁ እንደሀገር የተያዘውን የገጠር ትራንስፎርሜሽን ከግብ የሚያደርስ ነው ብለዋል። አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተጠቃሚ እና አሳታፊ የሆነ ሥርዓት እንደሚዘረጋ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ምቹ አገልግሎት አግኝተናል - ተገልጋዮች
Jun 17, 2026 834
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ በተደረገው የተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰራር ፈጣን፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት በይፋ ተመርቆ ሥራ መጀመሩ ይታወቃል፡፡ ይህ ዘመናዊ አሠራር ነዋሪዎች ወደ ተለያዩ የመንግሥት ቢሮዎች መሄድ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት አካባቢ ሆነው ጉዳያቸውን በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ መፈጸም እንዲችሉ ምቹ ዕድል ፈጥሯል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች እንደገለጹት፤ አዲሱ የዲጂታል ተንቀሳቃሽ መሶብ አሠራር ቀደም ሲል የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችና እንግልቶች ያስቀረ ነው። ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል አቤል አለማየሁ እንደገለጸው የአገልግሎት የነዋሪነት መታወቂያውን በተንቀሳቃሽ መሶብ በ10 ደቂቃ ውስጥ ማሳደስ መቻሉን ተናግሯል። ማንኛውንም አገልግሎት በአንድ ቦታ ማግኘት መቻሉ ጊዜን ለመቆጠብ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም አስታውቋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ መስፍን ተርፋ በበኩላቸው ቀደም ሲል መሰል ጉዳይ ለማስፈጸም ከሥራ ቀርተው ወደ ወረዳ ቢሮዎች በተደጋጋሚ ይመላለሱ እንደነበር አስታውሰዋል። አሁን ግን በሻይ ዕረፍታቸው ወቅት በመምጣት በ5 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። የማዕከሉ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ባለሙያ ዳኜ መኮንን እንደተናገሩት፤ ከአስፈጻሚ ኤጀንሲዎች ጀምሮ እስከ ክፍለ ከተማና ወረዳ ያሉ መዋቅሮች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እርስ በእርስ በተናበበ ሁኔታ እየተሰራ ይገኛል። መንገድ ፈንድና ፋይዳ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ባለሙያ እዝቹአለም ሲሳይ በበኩላቸው አሠራሩ ሕብረተሰቡ ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ቦታ እንዲያገኝ የሚረዳ ነው ብለዋል። አገልግሎቱ ተንቀሳቃሽ መሆኑ ደግሞ ነዋሪዎች እግረ መንገዳቸውን እንዲጠቀሙበት ዕድል በመፍጠሩ፣ በርካታ ተገልጋዮች በሥራው ተደስተውና አመስግነው እየሄዱ መሆኑን አስታውቀዋል። ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት አስተባባሪ ዳኛቸው ተፈራ፤ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል። አገልግሎቱ ሥራ ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በከተማዋ በሚገኙ ሁሉም ክፍለ ከተሞች በመዘዋወር አገልግሎት መስጠቱን አስታውቀዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ለመንግሥት ግዥ ሥርዓት ውጤታማነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል
Jun 17, 2026 522
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ለመንግሥት ግዥ ሥርዓት ውጤታማነት፣ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የፌዴራል ንብረትና ግዥ ባለስልጣን አስታወቀ። በበጀት ዓመቱ ባለፉት 11 ወራት ከ370 ቢሊዮን ብር በላይ በኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት መፈፀሙም ተጠቅሷል። የፌዴራል ንብረትና ግዥ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባለፉት 11 ወራት የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማጠናከርና የተቋማትን አቅም ለማጎልበት የአሰራር ሥርዓቶችን በማዘመን ረገድ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል። በአስተዳደር ስርዓቱ ውስጥ የአዋጅ መሻሻል እንዲሁም የመመርያዎቹ መውጣት ተከትሎ መዘጋጀት ያለባቸው መደበኛ የጨረታ ሰነዶችና ማንዋሎችን እንዲሁም የአሰራር ስርዓቶችን በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል። በዚህም 41 የሚሆኑ መደበኛ የጨረታ ሰነዶች በማዘጋጀት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ የተደረገ መሆኑን ገልጸው፤ 32ቱ የፌዴራል የመንግስት ግዥና ንብረት ሽያጭ የሚፈፀምባቸው መደበኛ የጨረታ ሰነዶች ሲስተም ውስጥ ተካተው ስራ ላይ ማዋል ተችሏል ብለዋል። በ2017 እና 2018 ሁሉም ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ግዥያቸውን የፈጸሙት በእቅዳቸው መሰረት እንደሆነ ገልፀው አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በየሩብ አመቱ እቅዳቸውን ማሻሻል የሚያስችል አማራጭ እንዳለው አንስተዋል። በበጀት ዓመቱ 367 የፌዴራል ባለበጀት መስሪያቤቶች ግዥያቸውን በኦንላይን እየፈፀሙ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ውስጥ ከ29 ሺህ በላይ ጨረታዎች ተካሂደው ከ370 ቢሊዮን ብር በላይ በኤሌክትሮኒክ ሥርዓት የተፈጸመ ሲሆን፣ ይህም ያልታቀደ ግዥን በማስቀረት የሕዝብና የመንግሥትን ሀብት ከብክነት ለመጠበቅ ትልቅ እገዛ አድርጓል ብለዋል። የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓት የተገልጋዮችን የጊዜ ብክነትና አላስፈላጊ የትራንስፖርት ወጪን በማስቀረት፣ ባሉበት ቦታ ሆነው የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ አስችሏልም ብለዋል። ይህ አሰራር ከሰዎች ንክኪ ነፃ በመሆኑ ለአቅራቢዎች፣ ለተወዳዳሪዎችና ለግዢ ፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የጎላ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን አስገንዝበዋል። መረጃን በቀላሉ ለሁሉም ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑም ተጠያቂነትን በማስፈን ብልሹ አሰራርን በከፍተኛ ደረጃ ለመከላከል የሚያስችል ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ለመንግሥት ግዥ ሥርዓት ውጤታማነት፣ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን አብራርተዋል። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስራዎችን በማጠናከር ተጠቃሚዎችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬትም ሥርዓቱን በክልሎች የማስጀመር ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው ምርታማነትን ለማላቅ የሚያስችሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ እያደረገ ነው
Jun 17, 2026 310
አዳማ ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ምርታማነትን ለማላቅ የሚያስችሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽ በማድረግ ለማህበረሰብ ተጠቃሚነት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ። የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፍቃዱ ምትኩ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው ምርታማነትን ለማላቅ የሚያስችሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽ በማድረግ ለማህበረሰብ ተጠቃሚነት እየሰራ ነው። ዩኒቨርሲቲው በተለይ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ለማሳካት የሚያስችሉ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ለአርሶ አደሩ የማድረስ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ለስራ አጥ ወጣቶችና ለአርሶ አደሩ የእርባታ ዶሮዎችን በማከፋፈል ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው በራሱ አቅም ጫጩቶችን በማስፈልፈል ለህብረተሰቡ ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ከ3 ሺህ በላይ ዶሮዎችን በማስገባት ወደ 40 ሺህ የሚጠጉ እንቁላሎችን ለገበያ እያቀረበ መሆኑን አስረድተዋል። የተሻሻሉ የወተት ላም ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ የተሻለ ሆርሞን ያላቸውን የኮርማ ዝሪያዎች በሰው ሰራሽ ስነ-ዘዴ በማዳቀል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል። በዚህም የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያን በማቋቋም የተሻለ ስራ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በሌላም በኩል ሶስት የተሻለ ምርት መስጠት የሚችሉ የስንዴ፣ የጤፍና የአጃ ሰብል ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረጉን ገልጸዋል። በዚህም ረገድ ከ1 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ መደረጉን የገለፁት ፕሬዚዳንቱ በአሁኑ ወቅት በበጋ መስኖ በ12 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ምርጥ ዘር ምርት እየተሰበሰበ ይገኛል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው የግብርና ልማት ስትራቴጂን ለመደገፍ እያከናወነ ከሚገኘው ተግባር ባሻገር ጤናማ ማህበረሰብን ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ እየሰራ እንደሚገኝም አክለዋል።
ማዕከሉ በምርምር ያወጣቸውንና ለቆላማ አካባቢዎች ተስማሚ የሆኑ የቡና ዝርያዎችን እያስፋፋ ነው
Jun 16, 2026 1442
ቴፒ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር ያወጣቸውንና ለቆላማ አካባቢዎች ተስማሚ የሆኑ የቡና ዝርያዎችን እያስፋፋ መሆኑን አስታወቀ። የምርምር ማዕከሉ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ አላሞ ቀበሌ ላይ በአርሶ አደሮች ማሳ ያላመዳቸውን የቡና ተክሎች ምልከታና የልምድ ልውውጥ አድርጓል። በማዕከሉ የሰብል ምርምር ሥራ ሂደት አስተባባሪ ሸሐሚል አሎ እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ከቡና ልማት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በምርምር ያወጣቸውን የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ የማላመድ ሥራ እየሰራ ነው። በምርምር የተገኙት ውጤታማ የቡና ዝርያዎችም በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡና ለቆላማ አየር ንብረት ተስማሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። የቡና ዝርያዎቹ በምርታማነታቸው የተረጋገጡ ከመሆናቸውም በላይ አርሶ አደሮች በጥራት በማምረት በገበያ ተወዳዳሪ የሚሆኑበትን እቅም እንደሚያጠናክሩም ጠቁመዋል። እነዚህ በምርምር የተገኙ "K-1"፣ "K-2" እና " I-2" የተሰኙ የቡና ዝርያዎች ምርታማነታቸው ከነባሩ ዝርያ በእጥፍ ከፍ ያሉ መሆኑን አስተባባሪው ገልጸዋል። የቡናው ዝርያ ውጤታማነት በማሳ ላይ በመረጋገጡ ወደ ሌሎች የአርሶ አደሮች ማሳ ለማስፋፋት ታቅዶ እንቅስቃሴ መጀመሩንም ተናግረዋል። በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ባለሙያ አቶ ፍስሐ ግዛው፤ በወረዳው የቡና አመራረትን በማዘመን የውጭ ምንዛሬ አቅምን ከፍ ለማድረግ ከምርምር ማዕከሉ ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። በወረዳው የአላሞ ቀበሌ አርሶ አደር ይንገሥ ጌታቸው ከምርምር ማዕከሉ የወሰዱትን የቡና ዝርያዎች በአምስት ሔክታር መሬታቸው ላይ እያለሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። የቡና ዝርያው በፍጥነት አድጎ ምርት ከመስጠቱ ባለፈ ለእንክብካቤና ለለቀማ ምቹ በመሆኑ ሥራውን ለማስፋፋት ከሚያደርጉት ጥረት ባለፈ ልምዳቸውን ለሌሎች አርሶ አደሮች እያጋሩ መሆኑን ጠቅሰዋል። ከማዕከሉ የተረከቡት የተሻሻለ የቡና ዝርያ ምርታማ በመሆኑ ነባሮቹን የቡና ማሳዎች በአዲስ እየተኩ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ አርሶ አደር ብርሃኑ ጌታቸው ናቸው። በተሻሻለ የቡና ማሳ ልማት ላይ ልምድ የወሰዱ አርሶ አደሮች በበኩላቸው እንዳሉት፤ በመስክ ምልክታው በቀጣይ የቡና ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የሚያስችል ተሞክሮ አግኝተዋል። ይህን ልምድ በመውሰድ ከዘንድሮ ክረምት ጀምሮ የተሻሻሉ የቡና ዝርያ ችግኞችን ከምርምር ማዕከሉ በመውሰድ ለመትከል መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ስፖርት
የዓለም ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ
Jun 18, 2026 92
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- በ23ኛ የፊፋ ዓለም ዋንጫ የስምንተኛ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በምድብ ሁለት ቼክ ሪፐብሊክ ከደቡብ አፍሪካ ምሸት አንድ ሰዓት ላይ በአትላንታ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በምድቡ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ቼክ ሪፐብሊክ በደቡብ ኮሪያ 2 ለ 1፣ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ የ2 ለ 0 ሽንፈት አስተናግደዋል። ሀገራቱ ከሽንፈታቸው ለማገገም እና ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋቸውን ለማለምለም ሶስት ነጥብ ማግኘት ይጠበቅባቸዋል። በዚሁ ምድብ ሜክሲኮ ከኮሪያ ሪፐብሊክ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ በጓድላሃራ ስታዲየም ይጫወታሉ። ከአዘጋጅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሜክሲኮ በመክፈቻው ጨዋታ ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ኮሪያ ሪፐብሊክ ቼክ ሪፐብሊክን 2 ለ 1 ማሸነፏ ይታወሳል። አሸናፊው ሀገር ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱን ያረጋግጣል። በምድብ ሁለት ስዊዘርላንድ ከቦስኒያ ሄርዞጎቪና ከምሽቱ አራት ሰዓት በሎስ አንጀለስ ስታዲየም፣ ካናዳ ከኳታር ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ በቢሲ ፕሌስ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ስዊዘርላንድ ከኳታር፣ ካናዳ ከቦስኒያ ሄርዞጎቪና በተመሳሳይ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ጨዋታው ሀገራቱ የመጀመሪያ ድላቸውን ለማስመዝገብ የሚያደርጉት ነው።
በዓለም ዋንጫው አፍሪካዊቷ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከፖርቹጋል ጋር አቻ ተለያየች
Jun 18, 2026 152
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ):- በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የምድብ 11 የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፖርቹጋል ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ውጤት ተጠናቋል። ትናንት ማምሻውን በሂውስተን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጆአኦ ኔቬስ በስድስተኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል ፖርቹጋል መሪ ሆናለች። የመጀመሪያው አጋማሽ ማብቂያ ላይ አሮን ዊሳ ከመረብ ላይ ያሳረፈው ጎል ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አቻ አድርጓል። ዊሳ ለኮንጎ በዓለም ዋንጫ ታሪክ የመጀመሪያውን ጎል በማስቆጠር ታሪክ ሰርቷል። ፖርቹጋል ከፍተኛ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ብትወስድም ሁለቱ ቡድኖች ተቀራራቢ የግብ እድሎችን ፈጥረዋል። ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ጎሏን ከማስቆጠር ባለፈ የመጀመሪያ ነጥቧንም አግኝታለች። አፍሪካዊቷ ሀገር ከ52 ዓመታት በኋላ ወደ ዓለም ዋንጫው መመለሷ ይታወቃል። የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዝዳንት ፍሊክስ ሼሲኬዲ በስታዲየሙ ተገኝተው ጨዋታውን በመከታተል ቡድኑን አበረታተዋል። ዓለም ዋንጫውን ያነሳሉ ተብለው ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ፖርቹጋል ነጥብ ጥላለች። ስድስተኛ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎውን ያደረገው አምበሉ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ41 ዓመት ከ132 ቀናት በመጫወት በውድድሩ ታሪክ በአንጋፋው እድሜ የተሰለፈ ተጫዋች መሆን አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል።
በተጠባቂው ጨዋታ እንግሊዝ ክሮሺያን አሸነፈች
Jun 18, 2026 124
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የምድብ 12 መርሐ ግብር እንግሊዝ ክሮሺያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። በዳላስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሃሪ ኬን በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ምት ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ጁድ ቤሊንግሃም እና ማርከስ ራሽፎርድ ቀሪዎቹን ጎሎች ለእንግሊዝ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ማርቲን ባቱሪና እና ፔታር ሙሳ የክሮሺያን ግቦች አስቆጥረዋል። ሀሪ ኬን በዓለም ዋንጫው ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 10 ከፍ አድርጓል። 115ኛ ጨዋታውን ለእንግሊዝ ያደረገው የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪው ኬን የጎል ብዛቱን 81 አድርሷል። በጨዋታው እንግሊዝ የተሻለ ብልጫ ወስዳለች። ውጤቱን ተከትሎ እንግሊዝ ምድብ 12ትን በሶስት ነጥብ መምራት ጀምራለች። ክሮሺያ ያለ ምንም ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዛለች።
ጋና ወሳኝ ድል ተቀዳጅታለች
Jun 18, 2026 125
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ጋና ፓናማን 1 ለ ዐ አሸንፋለች። ከእኩለ ሌሊት በኋላ በቶሮንቶ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ 12 ሁለተኛ ጨዋታ የ20 ዓመቱ የአማካይ ተጫዋች ካሌብ ይሬንኪ በ95ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል። ጋና የጨዋታ ብልጫ ቢወሰድባትም ወሳኝ ሶስት ነጥብ አግኝታለች። ተጋጣሚዋ ፓናማ በኳስ ቁጥጥር እና ግልጽ የግብ እድሎችን በመፍጠር ተሽላ ብትገኝም ጎል ማስቆጠር ተስኗታል። የጋናው አንቶዋን ሴሜኒዮ የጨዋታው ኮከብ በመባል ተመርጧል። ውጤቱን ተከትሎ የምዕራብ አፍሪካዋ ጋና ውድድሩን በድል ጀምራለች። ፓናማ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኳ የመጀመሪያ ነጥቧን የማግኘት ህልሟ ሳይሳካ ቀርቷል። በምድብ 12 ትናንት ማምሻውን በተካሄደ የመጀመሪያ ጨዋታ እንግሊዝ ክሮሺያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። በምድቡ ሁለተኛ መርሐ ግብር ጋና ከእንግሊዝ የምታደርገው ጨዋታ ይጠበቃል። ፓናማ ከክሮሺያ ሌላኛው የሚደረግ ጨዋታ ነው።
አካባቢ ጥበቃ
የኢትዮጵያን አስደናቂ የአረንጓዴ ዐሻራና የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ሊተገብሩት ይገባል
Jun 18, 2026 66
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ተሞክሮ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ሊሰፋ እንደሚገባ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ኦፊሰር ቻርለስ አኮል ገለጹ። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የአካባቢ መራቆትን ለመግታትና የውሃ ሃብት ዘላቂነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤቶች እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ ባደረጉት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተመሳሳይ የ2018 የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን በይፋ ያስጀመሩ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ 8 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ መጣሉን አስታውቀዋል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ኦፊሰር ቻርለስ አኮል ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብር የተጎዱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ እያደረገ የሚገኝ ኢኒሼቲቭ ነው። በዘላቂ ውሃ አጠቃቀም ላይም መርሃ ግብሩ ትርጉም ያለው ውጤት እያመጣ መሆኑን ተመልክተናል ያሉት ኦፊሰሩ፤ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራና አካባቢ ጥበቃ ላይ የሚደነቅ ሥራ እያከናወነች ነው ብለዋል። የደን ሽፋንን ማሳደግ የውኃ ሀብትን በዘላቂነት ለመጠበቅ ተጨባጭ ማሳያ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ የደን ሽፋንን ለማሳደግ ፈጣንና ሁሉን አቀፍ ሥራዎች እየተገበረች መሆኑን ተመልክቻለሁ ነው ያሉት። የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ተሞክሮን ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሊተገበሩት እንደሚገባ ጠቁመው፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ተሞክሮ ወደ ሌሎች ሀገራት እንዲሰፋ እያደረጉት ያለውንም ጥረት አድንቀዋል። በአፍሪካ የአካባቢ ጥበቃን ለማሳለጥ “ታላቁ የአፍሪካ አረንጓዴ ግንብ” የተሰኘ መርሃ ግብር መኖሩን አስታውሰው፤ ይህን መርሃ ግብር ከኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ጋር ማቀናጀት ለአህጉራዊ አካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው ብለዋል። የአረንጓዴ ልማቱን ማስፋፋት በአፍሪካ ያለውን የውሃና የመሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ከማሻሻሉ በላይ ለስራ እድል ፈጠራና ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
በመዲናዋ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ለፍራፍሬ ችግኞች ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል
Jun 18, 2026 76
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ለዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የፍራፍሬ ተክሎችን በስፋት ያካተቱ አምስት ሚሊየን ችግኞች መዘጋጀታቸውን የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ግርማ ሰይፉ ገለጹ። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት ከ2011 ዓ.ም. ጀምሮ በተከታታይ ባከናወነችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር እስካሁን 48 ቢሊየን ችግኞችን መትከል ችላለች። የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሀገራዊ ሕልሟ ጋር የተቆራኘ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበበት ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በቢሾፍቱ በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት፣ በዘንድሮው ዓመት ብቻ ስምንት ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተቀምጧል። አባቶቻችን በአድዋ ላይ ታሪካዊ ገድል ፈጽመው ሀገር እንዳስረከቡን ሁሉ፣ የአሁኑ ትውልድም በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ሌላኛውን የአረንጓዴ አርበኝነት ገድል እየደገመ ይገኛል። ይህ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ የሚፈጥረው የአየር ንብረት ለውጥ የመቋቋም አቅምና የምግብ ሉዓላዊነት ስኬት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ሉዓላዊነቷ የተረጋገጠና የበለጸገች ሀገር ለማስረከብ ለተጀመረው ጉዞ እንደ ትልቅ ምሰሶ የሚቆጠር ነው። የአዲስ አበባ ከተማ የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ግርማ ሰይፉ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በመዲናዋ ዘንድሮ ለሚከናወነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የዝግጅት ሥራ ተጠናቋል። በአሁኑ ወቅትም የችግኝ ማፍላትና የቦታ መረጣ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በከተማዋ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች የፅድቀት ምጣኔ በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን ጠቁመው፣ በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የፍራፍሬ ችግኞችን በስፋት ያካተቱ አምስት ሚሊየን ችግኞች እንደሚተከሉ አስታውቀዋል። በመሆኑም ወጣቶች እና ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በዘንድሮው የችግኝ ተከላና እንክብካቤ ሥራ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል። በሱሱኒ ችግኝ ጣቢያ የዘር ብዜትና የችግኝ እንክብካቤ ባለሙያ ተሾመ ፉፋ እንደገለጹት በጣቢያው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብርን ስኬታማ ለማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት መደረጉን አንስተዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በጣቢያው አንድ ነጥብ አምስት ሚሊየን ችግኞች ለተከላ ዝግጁ የተደረጉ ሲሆን በርካታ የተዳቀሉ የፍራፍሬ ዘር ችግኞች መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል። ችግኞቹ ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ ተከታታይ ክትትልና እንክብካቤ እንደሚያስፈልጋቸው የተናገሩት ደግሞ ሌላኛዋ ባለሙያ የሆኑት ፅጌ ነጋ ናቸው። አረንጓዴ ዐሻራን ከግብ ለማድረስ ችግኝን መትከል ብቻ ሳይሆን ተገቢውን እንክብካቤ ማድረግም ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የደን ሃብት ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ የከርሰና ገጸ ምድር ውሃ መጠን እንዲጨምር አስችሏል
Jun 18, 2026 130
ባህር ዳር፤ ሰኔ 11/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የደን ሃብት ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ የከርሰና ገጸ ምድር ውሃ መጠን በመጨመር የመስኖ ልማትን ለማሳደግ ማገዙን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ። የቢሮው ምክትል ሃላፊ ወይዘሮ መሰሉ ብርሃኑ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በክልሉ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ትግበራ የደን ሃብት ሽፋኑን ከማሻሻል በተጨባጭ የአፈር መከላትን መከላከል አስችሏል። እንዲሁም የክልሉን የደን ሃብት ሽፋን ከ14 ነጥብ 6 በመቶ ወደ 18 ነጥብ 9 በመቶ ማሳደግና የከርሰ ምድርና ገፀ ምድር ውሃ ሀብትን በማሳደግ የመስኖ ልማትን ለማሳደግ ማገዙን ጠቁመዋል። ዘንድሮም ተግባሩን በማስቀጠል የክረምት ወቅት የፍራፍሬ፣ የውበት፣ የደንና ሌሎች ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። ችግኝ ተከላውን በ261 ሺህ 460 ሄክታር መሬት ላይ ለማከናወን የጉድጓድ ቁፋሮ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል። በዚህ ዓመት ለሚከናወነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ውጤታማነትም በየደረጃው የሚገኘው አመራር፣ ወጣቶችና ሴቶች ብሎም መላው ህብረተሰብ በባለቤትነት እንዲሳተፍም ጠይቀዋል። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ሃላፊ የሰውዘር ደመላሽ በበኩላቸው በከተማው ለሚከናወነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞች ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል። ችግኞቹን ለመትከል የቦታ ልየታን ጨምሮ የመትከያ ጉድጓድ ቁፋሮ መከናወኑን ገልፀው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ላላቸው፣ ለደን እና ለውበት የሚሆኑ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በችግኝ ማፍላት ለተሰማሩ ወጣቶች መልካም አጋጣሚ በመፍጠር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረጉን የገለፀው ደግሞ በባህር ዳር ከተማ በችግኝ ማፍላት ስራ ላይ የተማራው ወጣት ንጉስ ቻሌ ነው። ሦስት ሆነው በመደራጀት ችግኞችን አፍልተው ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሶ፤ በዚህ ዓመት ለሚከናወነው ችግኝ ተከላም 70 ሺህ ችግኞችን ማዘጋጀታቸውን ገልጿል።
በጋሞ ዞን ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል
Jun 17, 2026 562
አርባምንጭ፤ ሰኔ 10/2018 (ኢዜአ)፦ በጋሞ ዞን በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የተፈጥሮ ሀብት ልማት ቡድን መሪ አቶ ስንታየሁ መኮንን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቭ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ልማት በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ነው። በዞኑ ለዘንድሮው የክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለፍራፍሬ፣ ለደን፣ ለጥምር ደን፣ ለእንስሳት መኖ የሚሆኑና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ በዞኑ በማህበራት፣ በቡድን፣ በፕሮጀክት፣ በመንግስትና በግለሰብ ደረጃ የሚለሙ 397 ችግኝ ጣቢያዎች መኖራቸውን ጠቅሰው አስፈላጊው ችግኝ በበቂ ሁኔታ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በዚህም ከ24 ሺህ ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት ላይ ተከላው እንደሚከናወን ጠቅሰው ለዚህም አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል፡፡ ለክረምቱ መደበኛና ለአንድ ጀምበር መርሃ-ግብሮች ስኬት የጉድጓድ ቁፋሮ ዝግጅት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መርደኪዮስ ኬርባ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር የሰው ልጅ ከእጽዋት ጋር ያለውን መስተጋብር በተጨባጭ ያሳደገ ነው ብለዋል። በተጨማሪም የአየር ሚዛንን በማስተካከልና የአካባቢን ስነ ምህዳር በመጠበቅ ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን ገልጸው በዘንድሮው ተከላም ህዝቡን በነቂስ ለማሳተፍ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም የችግኝ ዝግጅትና የጉድጓድ ቁፋሮ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ልማት የሚያስገኘውን ጥቅም ህብረተሰቡ በአግባቡ እየተረዳ መምጣቱን የገለጹት ደግሞ በምዕራብ አባያ ወረዳ የኡጋዮ ቀበሌ አርሶ አደር ጀማል አንጃ ናቸው። በተለይ እስካሁን በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች የተጎዱ መሬቶች እያገገሙ፣ የደረቁ ምንጮች እየፈለቁና የሙቀት መጠን ሚዛኑ እየተስተካከለ መምጣቱን በተጨባጭ እያየን ነው ብለዋል። በመርሃ ግብሩ የሚተከሉ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች አካባቢን ከመጠበቅ ባለፈ ለምግብነትና ለኢኮኖሚ ምንጭነት እያገለገሉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። በየጊዜው በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ሲሳተፉ መቆየታቸውን ጠቅሰው በዘንድሮው ዘመቻ ሙሉ ቤተሰባቸውን በማስተባበር ለችግኝ ተከላው መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 9107
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 7195
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 6016
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 5922
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
Jun 15, 2026 1141
በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 👉የተራሮች ስር ፈርጥ - ወልዲያ የዛሬው የወፍ በረር ምልከታችን የሚጀምረው የተራሮች ስር ፈርጥ በሆነችው ወልዲያ ከተማ በመገኘት ነው። ከደሴ በ120 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውና በረጃጅም ተራሮች የተከበበችው ወልዲያ ከተማ ከነበረችበት ጉስቁልና ወጥታ አሁን ላይ በውበት ፈክታ ትገኛለች። በሳምንቱ በዚህች ከተማ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኮሪደር ልማቷንና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፤ ተዘዋውረውም ጎብኝተዋል። በተለያዩ ታሪካዊና ባህላዊ ትውፊቶች ስሟ ጎልቶ የሚጠራው ወልዲያ እንደ ከዋክብት ፈክታ እንግዶቿን ተቀብላ አስተናግዳለች። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ገጠር ጭምር እየተስፋፉ መሆኑን አንስተው በቀጣይ ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ትገሰግሳለች ብለዋል። 👉የሸደር አዳሪ ትምህርት ቤት የሚቀጥለው መዳረሻችን በሶማሊ ክልል ፋፈን ዞን አውበሬ ወረዳ ሼደር ከተማ አዲስ የተገነባውን አዳሪ ትምህርት ቤት መመረቅ ይሆኗል። የትምህርት ቤቱን ግንባታ መርቀው ስራ ያስጀመሩት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ናቸው። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸው፤ በክልሉ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋት የተማረ ትውልድ ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በ138 ሚሊየን ብር የተገነባው ዘመናዊ ትምህርት ቤት ስራ መጀመሩ ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል። 👉የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የበረራ ቅኝታችን ቀጥሎ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በመስኖ እየለማ ያለ የስንዴ ምርት የመጎብኘት እድል አግኝተናል። በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን ቂምቢቢት ወረዳ በ21 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የመስኖ ስንዴ ሰብል መሰብሰብ ተጀምሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ፤ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የበጋ መስኖ ልማት ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም የአርሶ አደሩን ገቢ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ይገኛል ብለዋል። የግብርና ሜካናይዜሽንን በስፋት በመጠቀም እንዲሁም ፈጠራን በማከል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣት ጥረቱ በተሳካ መልኩ መቀጠሉን አንስተዋል። 👉ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ዓለም አቀፍ ክስተት ነው። ችግሩ በተለይም በታዳጊ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ሰብአዊ ጉዳቶችን እያስከተለ ይገኛል። ኢትዮጵያም የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደመሆኗ መጠን ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ መፍትሄ ለመስጠት ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች። በዚህ ረገድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት በሚከናወኑ ሥራዎች በምርምር እያገዙ ናቸው። በሂደቱ ውጤታማነት ላይ የሚመክር መድረክ በሰመራ በተደረገበት ወቅት የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲዎች የሕግና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲኖች ችግሩን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት በምርምርና በማማከር እያገዙ መሆናቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የሰዎች ህገወጥ ዝውውርንና ፍልሰትን ለመግታት የነፃ የሕግ ድጋፍና የማማከር አገልግሎትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ለህብረተሰቡ እየሰጡ ናቸው። 👉የኢትዮጵያ እያመረተች ነው በአማራ ክልል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር «ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሃ ግብሩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እና ሌሎችም በተገኙበት ተካሂዷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የገቢ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ ለውጭ ምንዛሬ አይነተኛ የገቢ ምንጭ መሆን አስችሏል ብለዋል። 👉መሶብ በአርባ ምንጭ፣ ዲላ እና ነቀምቴ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች እየተስፋፋ የመጣው የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት በዚህ ሳምንት አርባ ምንጭ፣ እና ዲላ ከተሞች ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። የመሶብ ማእከላቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀዋል። የዲጅታል አሰራርን በማስፋት ለዜጎች ፈጣንና የተቀላጠፈ አገልግሎት የመስጠት ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። 👉ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ በመጠለያ የሚገኙ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩ ስለመሆኑ ያነሳል። በመሆኑም ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን አደራጅቷል። በመሆኑም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በእለቱ ድምፅ መስጠት ካልቻሉት መካከል የሰሜን ምስራቅ ዕዝ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀናት በፊት ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፃቸውን ሰጥተዋል። በተመሳሳይ በአፋር ክልል እና በደብረ ብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያዎች የሚገኙ ዜጎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል። 👉የመኸር እርሻ ንቅናቄ በሲዳማ ክልል የመኸር እርሻን በንቅናቄ በመምራት የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡና ገበያን የሚያረጋጉ የግብርና ልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በንቅናቄ መድረኩ ርእሰ መስተዳደር ደስታ ሌዳሞ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት መሬት ጦሙን እንዳያድርና ግብአትን በወቅቱ በማቅረብ እንዲሁም ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት በመስጠት ምርታማነቱን ማሳካት አስችሏል። ዘንድሮም ተግባሩን በማስቀጠል የበልግ ሰብልን ከመሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻን ውጤታማ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። ይህም የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፍ በማምረት ገበያን ለማረጋጋትና ለኢንደስትሪዎች ግብአት ለማቅረብ ያስችላል ነው የተባለው። በምርት ዘመኑ የተያዘውን እቅድ ለማሳካትም አመራሩ ህብረተሰቡን በማስተባበር ለውጤቱ መትጋት እንዳለበትም በውይይቱ ተነስቷል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምርጥ ዘር ብዜትን በዓይነት፣ በመጠንና በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ ተችሏል። ቢሮው በግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ እና በክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የዘር ብዜት ዕቅድ አፈጻጸምና ዝግጅት ላይ ያተኮረ የባለ ድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የግብርና ግብዓትና ገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ እንደገለጹት፤ በክልሉ የምርጥ ዘርን በጥራትና በመጠን ለአርሶ አደሩ በወቅቱ በማድረስ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል። ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ ለኢንዱስትሪዎች በቂ ግብዓትን ለማቅረብና የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር አግዟል። ተግባሩን በማስቀጠልም በ2017/18 የምርት ዘመን በክልሉ ከ2 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከ30 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ማምረት መቻሉንም ገልጸዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት
Jun 14, 2026 1065
በኢዜአ ዐይን …! በሙሴ መለሰ አረንጓዴ ዐሻራ - ለዓየር ንብረት ለውጥ ላለመበገር የሚደረግ ትጋት የዓየር ንብረት ለውጥ የምድራችን ፈተና ነው። ልብ መባል ያለበት ግን አፍሪካ ለዓየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዋ አነስተኛ ሆኖ ሳለ ጉዳቷ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ስለዚህ አኅጉሪቱ ዕጇን አጣጥፋ ወቃሽና ጠባቂ ከመሆን ይልቅ፤ በፈተና ውስጥ ሆናም በዘላቂነት የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባት። የሩቅ መፍትሔ አይጨበጥም፤ አይዘልቅምና። ከመፍትሔዎች አንዱ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ነው።በዚህ ሂደት ደግሞ የኢትዮጵያ ድንቅ ስራ የሚወደስ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት፤ በ2011 ዓ.ም በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ለዓየር ንብረት ለውጥ ከተሰጡ ምላሾች መካከል በፊትአውራሪነት ይጠቀሳል። መርሐ-ግብሩ የጋራ ነው በሚል ዕሳቤ በርካቶችን በንቃት አሳትፎ ለዓለም የሚደርስ የዓየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር ዐሳይቷል። የደን ሽፋን መጠንን አሳድጓል። ይህም በዓየር ንብረት ለውጥ ላይ የራሱን ሚና እያበረከተ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የአረንጓዴ ዐሻራ ሚና ልቆ ይነሳል። ይህም የተራቆተ መሬትን ወደ ነበረበት ከመመለስ፣ የውኃ ሀብት አሥተዳደርን ምቹ ከማድረግ እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ጋር የሚያያዝ ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብሩ በዕድሜ፣ በጾታ፣ በትምህርት ደረጃ፣ በሥራ ዘርፎች፣ በኑሮ ደረጃ፣ በሐይማኖት ሳትለይ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች እንዲሳተፉበት በማድረጓ በዘርፉ ስኬታማ ጉዞ ላይ ናት። ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀት ከመሆን አልፎ ለጎረቤቶቿ ችግኝ በመለገስ መርሐ-ግብሩ እንዲስፋፋ እየተጋችም ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ሲናገሩ፤ አረንጓዴ ዐሻራ ኢትዮጵያ ትላልቅ ነገር አስባ፣ ትላልቅ ነገር ተልማ፣ ትላልቅ ነገር አቅዳ እና ሕዝቦቿን አስተባብራ ማሳካት እንደምትችል ለሌሎቹ ማሳያ ነው ማለታቸውም ከላይ ያነሳነውን ሐሳብ ያዳብረዋል። በተጨማሪም አረንጓዴ ዐሻራ በልዩ ትኩረት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሳይቆራረጥ እየተሠራ መሆኑን፤ በየዓመቱም በሚተከሉ ችግኞች ብዛት፣ በሚተከልበት መሬት ስፋት እና በሚሳተፉ ታታሪዎች ቁጥር እያደገ መሆኑን ያመላክታል። በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች እየወጡ በችግኝ ተከላ መሳተፋቸው የሀገርን የጋራ ራዕይ ለማሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መናገራቸው ይታወሳል። #አረንጓዴ_ዐሻራ #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 5046
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 9812
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
ትንታኔዎች
የጡት ካንሰርን ለመከላከል …
Jun 16, 2026 1206
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለጡት ካንሰር ላለመጋለጥ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ስለ አጋላጭ ምክንያቶቹ እንዲሁም ምልክቶቹና ሕክምናው የካንሰር ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ቢኒያም ተፈራ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ - ካንሰር እንዴት ይከሰታል? እንደ ዶክተር ቢኒያም ገለጻ፤ ጤናማ የሰው ልጅ በሕይዎት ዑደት ሲያልፍ በሰውነቱ ውስጥ ያሉ ኅዋሶች (ሴሎች) በመደበኛ ሁኔታ ይራባሉ፤ ጊዜያቸውን ጠብቀውም ይሞታሉ። ይህን ሂደት በተፈጥሮ መቆጣጠር የሚቻልና የራሱ የሆነ የመቆጣጠሪያ መንገድ ያለው መሆኑንም ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ በአንዳንድ ምክንያቶች (በዘረመል ለውጥ ወይም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ሊሆን ይችላል)፤ ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ መራባት ሲጀምሩና ወይም መሞት ባለባቸው ጊዜ ሳይሞቱ ሲቀሩ፣ በራሳቸው አካባቢ ከመጠን በላይ በማደግ እንደ ዕጢ ያለ ነገር ሲፈጥሩ፤ ከዚህ አልፎ በአካባቢያቸው ያሉ ኦርጋኖችን መያዝ ሲጀምሩ እንዲሁም ወደ ሌላ የሰውነት አካል በመሄድ ባልተፈቀደላቸው ቦታ ላይ ማደግና ያለቁጥጥር መራባት የሚጀምሩበት ሂደት ካንሰር ተብሎ ይጠራል። ካንሰር ስሙ የሚሰየመው እንደተከሰተበት የሰውነት ክፍል መሆኑን አስገንዝበው፤ የጡት ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የቆዳ ካንሰር … እየተባለ የሚጠራው በዚሁ አግባብ መሆኑን አስረድተዋል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድናቸው? እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ቨርቹዋል ኦቲዝም የጡት ካንሰር ምልክቶች በጡት ውስጥ ቀደም ሲል ያልነበረ (አዲስ) ዕብጠት መከሰት፣ የጡት ቆዳ ቀለም መለወጥ፣ ቁስለት መኖር፣ ከጡት ጫፍ ላይ መግል ወይም ደም መሰል ፈሳሽ መውጣት፣ በብብት ሥር አካባቢ የሚከሰት ዕብጠት በአብዛኛው የጡት ካንሰር ምልክቶች መሆናቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ምልክቶች ኬዙ አድጎ መታየት ሲጀምር የሚስተዋሉ መሆናቸውን በመጠቆም፤ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ምልክቶች ሳይኖሩ የጡት ካንሰር የመያዝ ዕድል መኖሩን አመላክተዋል። ወደ ጤና ተቋም መቼ መሄድ ይመከራል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ በአጠቃላይ አንዲት ሴት ጡቷ ላይ ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ለውጥ ካለ ካንሰር ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል በመገመት ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ይጠበቅባታል። ነገር ግን ከካንሰር ጋር በተያያዘ ጥርጣሬን ሊጨምሩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመው ከነዚህም አንዱ በጡት ውስጥ ዕብጠት መኖርና ዕብጠቱም ምንም ዓይነት ህመም የሌለው መሆንን ጠቅሰዋል። አክለውም እስከ 80 በመቶ የሚሆነው በዕብጠት የሚመጣ የጡት ካንሰር ህመም እንደሌለው አንስተዋል። ህመም የለውም ብሎ ዕብጠትን ችላ ማለት እንደማይገባም በመምከር። በአጠቃላይ አንዲት ሴት ከላይ የጡት ካንሰር ምልክቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ካየች በአፋጣች ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚጠበቅባት በአጽንዖት ገልጸዋል። በተጨማሪም በአጠቃላይ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ጡታቸውን እየዳበሱ ከወትሮው የተለየ አዲስ ምልክት መኖሩን ማየት እንዳለባቸው መክረው፤ የተለየ (አዲስ) ነገር ሲኖር ወደ ሕክምና እንዲሄዱ አሳስበዋል። የአሳሳቢነት ደረጃ የጡት ካንሰር በጣም አሳሳቢ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ ከካንሰር ዓይነቶች ሁሉ በሀገራችን በቀዳሚነት ይቀመጣል ብለዋል። በተለይም ይላሉ፤ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች 1/3ኛ (31 በመቶ ገደማ) ያህሉ የጡት ካንሰር ነው። በእርግጥ ወንድንም ሴትንም ብንደምረው በብዛትም ሆነ በሽታ በማስከተል ረገድ በአንደኝነት የሚቀመጥ ነው ይላሉ። ስለ ጡት ካንሰር ያለ ግንዛቤ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጡት ካንሰር አጠቃላይ ሁኔታዎች ሰፊ የግንዛቤ እጥረት መኖሩን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2/3ኛ በላይ የሚሆነው ታማሚ ወደ ሕክምና ተቋም የሚመጣው በሽታው በጣም ሥር ከሰደደ በኋላና ችግር መፍጠር ሲጀምር መሆኑን አንስተዋል። በወቅቱ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሄዱት ሴቶች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን (ከ30 በመቶ በታች) መሆኑንም አመላክተዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ብለዋል። በመንግሥታዊና በግል ተቋማት ጭምር ለአብነት የጥቅምት ወርን የጡት ካንሰር ወር አድርጎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም በቂ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም ስለጡት ካንሰር በአግባቡ አለማወቅ እንዲሁም በጡት ላይ የሚስተዋሉ ምልክቶችን ልብ አለማለት (ቀለል አድርጎ በማሰብ ሥር እንዲሰድ ዕድል መስጠት) እንዳለ አብራርተዋል። በጡት ካንሰር የሚከሰት ሞትን ከፍ ከሚያደርጉት አንዱ የግንዛቤ እጥረት እንደሆነ ይታመናል ይላሉ። በወንዶች ላይ የጡት ካንሰር በወንዶች ላይም የጡት ካንሰር ሊከሰት እንደሚችል የሚናገሩት የሕክምና ባለሙያው፤ የሚከሰትበት መጠን (ቁጥር) ግን በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ነው ያስረዱት። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ላይ ቁጥሩ በዛ ቢልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ1 በመቶ በታች መሆኑንም ገልጸዋል። ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ ወንዶች ላይ እንደሚከሰት በመግለጽ፤ ወንዶች በጡታቸው ላይ የተለየ ምልክትና ህመም ሲሰማቸው ወደ ሕክምና መሄድ እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል። የጡት ካንሰር በሕጻናትና አዳጊዎች ላይ አይከሰትም ብሎ መደምደም ባይቻልም፤ የመከሰት ዕድሉ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ዶክተር ቢኒያም አስረድተዋል። እዚህ ላይ ብዙም አያሳስብም ይላሉ። ዕድሜና የጡት ካንሰር በአብዛኛው የጡት ካንሰር የሚከሰተው ዕድሜ እየጨመረ ሲሄድ መሆኑን የሚገልጹት ዶክተር ቢኒያም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍ እንደሚል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አብዛኛው ሕዝብ ወጣት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው፤ ከ70 እስከ 80 የሚሆኑት የጡት ካንሰር ታማሚዎች ከ30 እስከ 50 ባለው ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ዕድሜያቸው ገፋ ባሉም ሆነ በወጣቶች ጡት ላይ አዲስ ህመም ሲስተዋልና ምልክት ሲታይ ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ እንጅ፤ ከ50 ዓመት በላይ በሆናቸው ሰዎች ላይ የሚከሰት ነው ብሎ ችላ ማለት ተገቢ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል። ለጡት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች እንደ ሕክምና ባለሙያው ማብራሪያ፤ የጡት ካንሰር እኛ ቀድመን ብንሠራባቸው ተጋላጭነትን የምንቀንስባቸው እና ከቁጥጥራችን ውጭ በሆኑ (ተፈጥሯዊ) ሁኔታዎች የምንጋለጥባቸው ጉዳዮች አሉ። ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት፣ አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ (ፕሮሰስ የተደረጉ) ምግቦችን ማዘውተር፣ አትክልትና ፍራፍሬ አለመመገብ ተጋላጭነቱን እንደሚጨምሩ አንስተዋል። እነዚህን በማስተካከል ተጋላጭነትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል። በተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ለጡት ካንሰር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች የዕድሜ መጨመር፣ ሴት መሆን፣ በዘረመል (በጀኔቲክ) ለውጥ (በቤተሰብ ወይም በሕይዎት አጋጣሚ ከአካባቢያዊ ሁኔታ የሚመጡ የዘር መለወጦች) ለጡት ካንሰር ሊያጋልጡ እንደሚችሉ አብራርተዋል። እነዚህን ምንም ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ መፍትሔው ምልክት (ጥርጣሬ) ሲኖር ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያውኑ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ ነው ይላሉ። ሕክምና እና የመዳን ተስፋ የጡት ካንሰር የመዳን ተስፋው ጥሩ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የሚወሰነው ግን ህመሙ እንደተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) ነው ይላሉ። [6/16/2026 9:29 AM] awe: በአጠቃላይ ሲታይም፤ ቶሎ ወደ ሕክምና በመሄድ የታከመ ካንሰር የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ባብዛኛው የሚሰጡ የሕክምና አማራጮችም፤ ኦፕሬሽን፣ ኬሞቴራፒ፣ የጨረር ሕክምና፣ የሆርሞን ሕክምና ሲሆኑ፤ አልፎ አልፎ ደግሞ እንደሁኔታው ታርጌትድ ቴራፒ እና ሚኖቴራፒ የሚባሉ የሕክምና አማራጮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። የሕክምና አማራጩን የሚወስነው በሽታው የተገኘበት ደረጃ (ስቴጅ) መሆኑንም አስገንዝበዋል። ምክረ ሐሳብ ሕብረተሰቡ እንዲገነዘበው የምንፈልገው ቶሎ ከታወቀ የጡት ካንሰር ታክሞ ይድናል፤ ለዚህ ደግሞ በጡት ላይ አዲስ ነገር ሲስተዋል ቶሎ ወደ ሕክምና መሄድ አዋጭ መሆኑን ነው ብለዋል። በጡት ላይ የሚስተዋል ዕብጠትና ህመም ሁሌም ካንሰር ነው ማለት ስላልሆነ ሴቶች ሳይደናገጡ ምርመራ እንዲያደርጉ መክረው፤ የምርመራ ውጤቱ ካንሰር መሆኑን ቢያሳይ እንኳ ቶሎ ወደ ሕክምና እስከሄዱ ድረስ በቀላሉ መዳን እንደሚችል መገንዘብ እንዳለባቸውም መክረዋል። ሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ከጡት ካንሰር ጋር በተያያዘ ከሚሰራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች መቆጠብ እንደሚገባውም ይመክራሉ። ቢያንስ ዕድሜያዋ ከ20 ዓመት በላይ የሆናት ሴት በወር አንድ ጊዜ ጡቷን በመዳበስ (ዕብጠትም ካለ እንዲታያት በመስታዎት ፊት ሆና በመመልከት) ቀደም ሲል ያልነበረ አዲስ ነገር መኖሩን መከታተል ይጠበቅባታል። ይህም ኬዙ ቢከሰት እንኳ ቶሎ ለመዳን ስለሚያግዝ ይላሉ። ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ደግሞ ቢቻል በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የጡት ቅድመ ምርመራ እንዲደርጉ መክረዋል። #ኢዜአ #የጡት_ካንሰር #የጤና_ነገር
በኢዜአ ዐይን…!
Jun 15, 2026 641
በዮሐንስ ደርበው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ • እንደ መነሻ ባሳለፍነው ወርኃ ግንቦት ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂዳለች። ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መታያ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ገቢራዊነት መገለጫ፤ ሕዝባዊ መንግሥትን አንባሪ ብሎም በሕዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደሥልጣን የሚመጣበት መንገድ ነው። ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ቁልፍ ነው። • ቅድመ ምርጫ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ባለድርሻ አካላት ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውነዋል። ለአብነትም፤ የምርጫ ሕጉን ከማሻሻል ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥርዓቶች ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል። በተጨማሪም የምርጫ ትምህርትና ግንዛቤን ለማስፋት ለሚሠሩ በርካታ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። የምርጫ ሂደትን ፍትሐዊነት ለማረጋገጥም በርካታ ድርጅቶች በታዛቢነት ተመዝግበዋል። የመራጮች ምዝገባም፤ በመደበኛ የመራጮች ምዝገባ (ማኑዋል)፣ ምርጫዬ በተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና በድረ ገጽ አማራጭ በመቅረቡ በርካታ መራጮችን አሳትፏል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በ24 ሬዲዮ፣ በ20 ቴሌቪዥን እና በ6 ጋዜጦች በሕዝብና በንግድ ሚዲያዎች ነጻ የአየር ሠዓት ተደልድሏል፤ ሐሳባቸውንም ተደራሽ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ በአረንጓዴ ዐሻራ ጸንቶና ተግቶ መሥራት ዘመኑ የሚፈልገው ዐርበኝነት • በምርጫ ወቅት በምርጫ ካርድ ሀገር የሚመራን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ ከሥልጣኔ መገለጫዎች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። የመራጮች ንቁ ተሳትፎም የሕዝቡን ዴሞክራሲያዊ ልምምድ ያጎለብታል። ምርጫ፤ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ፣ ተቋማዊ አሠራሮች እንዲጠናክሩ ቁልፍ በመሆኑ ጠቅላላ ምርጫው ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት ነው። የሕዝቡን ትጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክትም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተዓምረኛም ሕዝብ ነው፤ ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባሕል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ታሪካዊ በሆነው ዕለትም፤ የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣ የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው፣ ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣ ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣ የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣ ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣ ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤ በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል ያሳዩት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ሁሉ የሥልጡን ሕዝብ ትጋት በኋላ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አረጋግጠዋል። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡ 00 ሠዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ረጃጅም ሰልፍ የነበረባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እስከ ሌሊቱ 6 ሠዓት በማራዘም መራጮች ድምፅ እንዲሰጡ መደረጉን አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ የ7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተመለከተ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እንደተጠቀሙበትም ልዑካቸው ታዝቧል። ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር አሳይተዋል፤ ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ መርጠዋል፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት ነው ብለዋል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ዐይተናል ብለዋል። የምርጫ ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ መካሄዱን፣ በምርጫ ጣቢያዎችም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ልጆቻቸውን የያዙ እናቶች፣ ወጣቶች እና አዛውንቶች ሳይቀሩ ከማለዳው ጀምሮ ድምጽ ሲሰጡ እንደነበር መታዘባቸውን ተናግረዋል። በሁሉም አካባቢ የድምፅ መስጠት ሒደቱ በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመጠቆም፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የታየበት መሆኑን አስታውቀዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዜጎች የነቃ ተሳትፎ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማስፈፀም ዐቅም እያደገ መምጣቱ የታየበት ስኬታማ ምርጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አሕመድ ሁሴን ናቸው። ምርጫውን መታዘባቸውን በመጥቀስ፤ ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምርጫው አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ድምጻቸውን እንደሰጡም ነው የገለጹት፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ይበልጥ አካታች ተሳትፎን እያጎለበተ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል። አክለውም፤ መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም አጋር አካላት ለምርጫው ስኬታማነት ሚናቸውን መወጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት እንዲጠናከሩ በትኩረት መሠራቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቦርዱ ነፃና ገለልተኛ በመሆን የማስፈጸም ዐቅሙ እያደገ መምጣቱን በማንሳት፤ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡ • ድኅረ ምርጫ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ የ1 ሺህ 8 የምርጫ ክልሎች ውጤት ወደ ቦርዱ የማረጋገጫ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል። የምርጫ ጣቢያዎች የውጤት ቆጠራ ተጠናቅቆ በምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል። ከ501ዱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች 446ቱ ወደ ማዕከል መድረሳቸውንና ቀሪዎቹ የክልል ምክር ቤቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመጠለያ ጣቢያዎችና በካምፖች የድምፅ አሰጣጥ መከናወኑን ጠቁመው፤ ውጤት የማዳመር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል። #ምርጫ #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #በኢዜአ ዐይን
ከአፍሪካ ሰማይ እስከ ዓለም ከፍታ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ!
Jun 12, 2026 5046
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው የኢትዮጵያ የዘመናት ስኬት መገለጫ፤የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል እና በኢንዱስትሪው በዓለም ስመጥር ተቋማት መካከል አንዱ ነው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ። አየር መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ኢትዮጵያን በአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ከፍ በማድረግ፣የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አየር መንገዱ ወደ ካይሮ "አንድ" ብሎ የጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ዛሬ ላይ በአምስት አኅጉራት 145 መዳረሻዎችና በ147 ዘመናዊ አውሮፕላኖች አገልግሎቱን እያቀላጠፈም ይገኛል። አየር መንገድ የገነባው ዐቅም በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉት ሲሆን የወደፊት ዕቅድና የዐቅም ግንባታ ትኩረቶቹ ለቀጣይ ስኬቱ ቁልፍ እንደሚሆኑም ይጠበቃል። በተለያዩ ጊዜያትም ዓለም አቀፍ፣አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሽልማቶችን መሰብሰቡ ለዚህ ሁነኛ አስረጂ ይሆናል።የበረራ አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት፤የተቋማዊ ዕድገቱን ማስቀጠል እንዳስቻለውም ይገለጻል። አየር መንገዱ በታላቅነቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመዝለቅ የሀገር ውስጥ አቅሙን ማሳደግ እና የነበሩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በማደስ፣በማስፋፋት፣በማዘመን፣አዳዲስ በመገንባት ክልሎችን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር ለዜጎቹ ምቹ ሁኔታ እንዲኖር በልዩ ትኩረት እየሠራ ይገኛል። በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡትን ስኬቶች በቴክኖሎጂውም ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው? የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻውን በቅርቡ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉም የእዚሁ ትጋት አንዱ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።ይህ መዳረሻ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ነው። ይህ መሠረተ-ልማትም ለአካባቢው ነዋሪ፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና ቱሪዝም ትልቅ ሥጦታ ነው። የምንገነባው እያንዳንዱ አዲስ የአውሮፕላን ማረፊያ ርቀትን በማጥበብ ትስስር ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ይህም የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ያነቃቃል እንዲሁም ሕዝባችንን ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። የአፍሪካ ኩራት የሆነውና 80ኛ ዓመቱን የያዘው አየር መንገዱ በእርግጥም “የአፍሪካ አዲሱ መንፈስ” (The New Spirit of Africa!”) ነው ሲሉ ገልጸውታል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላን፣ የበረራ መዳረሻ በማስፋትና በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማት ግንባታ አስደናቂ ሥራ እየሠራ ነው። በሰፊ የአውታረ መረብ መስመሮች በርካታ ሀገራትን ተደራሽ በማድረግ ግንባር ቀደም ከሚባሉት ጥቂት አየር መንገዶች አንዱ ለመሆንም በቅቷል። አየር መንገዱ መንገደኞችን ከሀገር ሀገር ከማዘዋወር፤ከፍተኛ የካርጎ አገልግሎትን ከማቀላጠፍ ባሻገርም በሀገራት መካከል ንግድን፣ቱሪዝምን፣ኢንቨስትመንትን እና ውህደትን በመፍጠር በኩል ለአመታት የዘለቀ ዝናን አትርፏል። ይህ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግንባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ባስጀመሩበት ወቅትም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህም የኢትዮጵያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስር ዘላቂ በማድረግ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋፕሮጀክት እየለማ ይገኛል ማለታቸው የዚሁ ማሳያ ነው። #በኢዜአ_ዐይን…! #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #Ethiopian_News_Agency
ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ምንድን ናቸው?
Jun 12, 2026 1659
የጤና ነገር … በዮሐንስ ደርበው የሰው ልጅ ሊሻሻሉ በሚችሉ እና በማይችሉ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ለልብ ህመም ሊጋለጥ እንደሚችል የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የአዋቂ የልብ ሕክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ብርሃኑ ሞገስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የልብ ህመም ከተወሳሰብ ዘላቂ የጤና እክል እስከ ድንገተኛ ኅልፈት ያደርሳል። ለልብ ህመም አጋላጭ መንስዔዎች ሰዎች ማሻሻል በሚችሏቸው (ሞዲፋይብል) እና ማሻሻል በማይችሏቸው (ነን ሞዲፋይብል ወይም ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች) ለልብ ህመም ሊጋለጡ እንደሚችሉ ዶክተር ብርሃኑ ይገልጻሉ። መሻሻል ከሚችሉ አጋላጭ ምክንያቶች መካከል፤ ከፍተኛ ጭንቀት፣ ሲጋራ ማጨስ፣ ከፍተኛ የደም ግፊት ህመም (በአግባቡ መድኃኒቱ ካልተወሰደ)፣ተገቢ ያልሆነ የስብ ክምችት፣ ከፍተኛ ውፍረት (ክብደት)፣ በቂ እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ጤናማ አመጋገብ አለመኖር እንዲሁም አብዝቶ ስኳር፣ ጣፋጭና አልኮል መጠቀም የሚሉትን ይጠቅሳሉ፡፡ እንዲሁም ሰዎች ማሻሻል ከማይችሏቸው (ተፈጥሯዊ) አጋላጮች መካከል፤ በቤተሰብ የሚተላለፍ መኖሩን፣ በዕድሜ መጨመር የሚከሰት መሆኑን (ለምሳሌ፡- ወንድ ከ45 ሴት ከ55 ዓመት በላይ ሲሆናቸው ለልብ ህመም ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩን) እንዲሁም ወንዶ ከሴቶች በይበልጥ ለልብ ህመም ተጋላጭ የመሆናቸው አጋጣሚ ሰፊ ሊሆን እንደሚችልም አብራርተዋል፡፡ በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም የልብ ህመም ምልክቶች የደረት ውጋት በግራ በኩል ወይም መሐል ላይ፣ ከወትሮው የተለየ ድካም፣ ትንፋሽ ማጠር፣ ከመደበኛው የተለየ የልብ ምት መኖር፣ የሰውነት በተለይም እግር አካባቢ እብጠት፣ ራስን መሳት እና ሳል የልብና ተያያዥ ህመም ምልክት ሊሆኑ እንደሚችሉ አብራርተዋል። የልብን ጤናን ለመጠበቅ በተቻለ መጠን ጤናማ አመጋገብን መከተል እንደሚገባ የሚመክሩት ዶክተር ብርሃኑ፤ አትክልት ማዘውተር፣ ምግብ ሲዘጋጅም ፈሳሽ ዘይት መጠቀም፣ ስኳር፣ ጨው እና ጣፋጭ ነገሮችን መገደብ ከተቻለም ማስወገድ እንደሚገባ ይመክራሉ፡፡ አካላዊ እንቅስቃሴ ማዘውተር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ ይህም ብስክሌት መንዳት፣ በእግር እንቅስቃሴ ማድረግ፣ ዋና መዋኘት፣ እስከሚያልብ እና የልብ ምት እስከሚጨምር ብሎም እስከሚደክሙ የአካል ብቃት መሥራት የልብን ጤና ለመጠበቅ አስተዋጽዖ አለው ነው ያሉት፡፡ ጤናማ የሰውነት ክብደት እንዲኖር ማድረግ ተገቢ መሆኑን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ “ቦዲ ማስ ኢንዴክስ (ቢ ኤም አይ)” ከ18 ነጥብ 5 እስከ 25 እንዲሆን ይመከራል ብለዋል፡፡ ሲጋራ አለማጨስ፣ አልኮል አለመጠቀም፣ የስኳር ህመምና ከፍተኛ ደም ግፊት ካለም የመድኃኒት አወሳሰድን አለማስተጓጎል፣ አመጋገብ ላይ ስብ አለማብዛትና አብዝቶ አለመቀመጥ የልብ ህመምን ለመከላከል እንደሚያግዙ ነው ያስረዱት፡፡ ዕድሜያቸው ከ45 ዓመት በታች የሆኑ ጤናማ ሰዎች ከአንድ እስከ ሦስት ዓመት ባሉ ጊዜያት አንድ ጊዜ፣ ዕድሜያቸው ከ45 በላይ የሆኑ በየዓመቱ እንዲሁም የልብ ህመም ያለባቸው እንደሁኔታው በየጊዜው ክትትል እንዲያደርጉም መክረዋል፡፡ ሰዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ እራሳቸውን ከልብ ህመም እንዲጠብቁ መክረው፤ ከዚህ ያለፈ ችግር ሲኖር ቶሎ የሕክምና ክትትል ማድረግ እና “ዛሬ ነገ” በማለት ጊዜ እያባከኑ ህመሙ ውስብስብ ደረጃ እስኪደርስ መጠበቅ እንደማይገባቸው አሳስበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ጤና #የልብ_ህመም
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና
Jun 17, 2026 440
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል። የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 15502
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 8589
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 14360
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 9812
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። የጡት ካንሰርን ለመከላከል … ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 7464
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !