ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል
Aug 11, 2026 26
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ አስታወቀ።   የቢሮው ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ለኢዜአ እንደገለጹት በግብርና፣ በአገልግሎት፣ በእንጨትና ብረታብረት እንዲሁም በሌሎች መስኮች የሥራ ዕድል በመፍጠር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተጀመሩ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል።   ቢሮው በ2018 በጀት ዓመት በግብርና፣ በአገልግሎትና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ለ400 ሺህ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ለመፍጠር አቅዶ ከ379 ሺህ 430 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ለመፍጠር መቻሉን ተናግረዋል። የሥራ ዕድል ፈጠራውን ውጤታማ ለማድረግም በበጀት ዓመቱ ከ925 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ብደር መመቻቸቱን፣ 8 ሺህ 420 ሄክታር መሬት መቅረቡን እና 689 አዳዲስና ነባር ሼዶች ለኢንተርፕራይዞች እንዲተላለፉ መደረጉን ተናግረዋል።   በበጀት ዓመቱ የሥራ እድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል በጉራጌ ዞን እምድብር ከተማ ነዋሪ ወጣት ዳዊት ትዛዙ እንዳለው ከመንግስት ባገኘው የገንዘብ ብድር በቅመማ ቅመም፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ መሰማራቱን ጠቁሟል። በአራት ሄክታር መሬት ላይ እያለማ ያለውን ቲማቲም ሽንኩርትና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን መጀመሩንም ተናግሯል።   በአሁኑ ወቅትም ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ሥራ አጥ ወገኖች ጊዜያዊ ሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ገልጿል። በመንግስት ካገኘው የገንዘብ ብድር በተጨማሪ በተሰማራበት የእርሻ ሥራ ውጤታማ እንዲሆን በግብርና ባለሙያዎች ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግለትም ተናግሯል። ሌላው በሆሳዕና ከተማ ነዋሪ ወጣት ዳንኤል አሰፋ በበኩሉ በከተማው በሚገኘው ታዴ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ኢንተርፕራይዝ ቋሚ የሥራ ዕድል እንደተፈጠረለት ገልጿል።   በዚህም በሚያገኘው ገቢ እራሱን ከማስተዳደሩ በተጨማሪ ነገ የራሱን ሥራ በመፍጠር ሕይወቱን የተሻለ ደረጃ ላይ ለማድረስ ራዕይ እንዲሰንቅ ማድረጉን ተናግሯል።  
በኦሮሚያ ክልል የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Aug 11, 2026 52
ጅማ ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የወጣቶች ክንፍ የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ረሂማ ዩሱፍ አስታወቁ። በጅማ ዞን በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በዞኑ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች የደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካሞች ቤት ዕድሳት እና ሌሎች የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች ተጠናክረው እየተከናወኑ ይገኛሉ።   በዛሬው ዕለትም በዞኑ ማና እና ጎማ ወረዳዎች ለአቅመ ደካማ ወገኖች በበጎ ፈቃድ የተለያዩ ድጋፎች ተደርገዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የወጣቶች ክንፍ የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ረሂማ ዩሱፍን ጨምሮ የጅማ ዞን አስተዳዳሪ ቲጃኒ ናስር እና ሌሎችም የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል። የተደረገው ድጋፍ የአቅመ ደካማ ወገኖችን ሕይወት በዘላቂነት ለመቀየር ያለመ መሆኑም ተገልጿል። ከተደረጉት ድጋፎች መካከል የትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ፣ የምግብ ግብዓት፣ የንብ ቀፎዎች እና ዘመናዊ የኤክትሪክ ምጣድ ይገኙበታል።   ወይዘሮ ረሂማ በወቅቱ፤ በክልሉ በርካቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቅሰው፤ በዚህ ውስጥ የወጣቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ሁሉም በያለበት በመተባበር በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚያደርገውን ተሳትፎ እንዲያጠናክርም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፤ በዘንድሮው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በዞኑ ከ5 ሺህ 500 በላይ የአቅመ ደካሞችን ቤት ለማደስ ታቅዶ እስካሁን ከግማሽ በላይ የሚሆኑት መታደሳቸውን ተናግረዋል።   የተደረገው ድጋፍ የዕለት ብቻ ሳይሆን ዘላቂነት ያለው መሆኑን የገለጹት አስተዳዳሪው፤ ድጋፉ የተደረገላቸው ወገኖች ሰርተው ሕይወታቸውን መለወጥ እንዳለባቸው አሳስበዋል። በማና ወረዳ በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር እስካሁን ከ300 በላይ የሚሆኑ የአቅመ ደካሞች ቤቶች መጠገናቸውን የገለጹት ደግሞ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሰመሩዲን አህመድ ናቸው።   ከዚህ በተጨማሪ የደም ልገሳ እና ሌሎችም ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እገዛ ብቻ ሳይሆን እንደ ገዳ ስርዓት ነባር የመተሳሰብ እና የመደጋገፍ ባህላችን ነው ብለዋል።   ድጋፍ ከተደረገላቸው መካከል የማና ወረዳ ነዋሪዎቹ ወይዘሮ ፋጡማ አባገሮ እና ትዕግስት ጌታቸው፤ የተደረገላቸው ድጋፍ የዕለት ጉርስ ብቻ ሳይሆን በዘላቂነት ህይወታቸውን የሚቀይር መሆኑ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል። በቀጣይ ሰርተው በመለወጥ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሌሎችን እንደሚደግፉ ቃል ገብተዋል።
በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል
Aug 11, 2026 79
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ ህገወጥነትን በመከላከልና በማጋለጥ በኩል ህብረተሰቡ ተሳትፎውን ማጠናከር እንዳለበትም ጠቁመዋል። መንግሥት በተደራጀ ሙስናና ሕገወጥ ድርጊቶች የተሰማሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል የሕግ የበላይነትን እያረጋገጠ እንደሚገኝ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በሰጠው መግለጫ አሳውቋል፡፡ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት ከልማት ሥራዎች ባሻገር የሕግ የበላይነትን ማስፈን ቀዳሚ ተግባሩ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ የመንግሥትን ሕግ የማስከበር ርምጃ በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ የህዝብን ሀብት ከምዝብራና ብክነት መጠበቅ የመንግሥት ትኩረት ሊሆን ይገባል፡፡ በቅርቡ መንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊቶች ላይ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ስር በማዋል ተጠያቂነትን ለማስፈን የወሰደው እርምጃ ተገቢና ቀጣይነት ሊኖረው የሚገባ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጭዎች መካከል ሄኖክ ተስፋዬ፤ ርምጃዎቹ የሕግ የበላይነትን በማስፈን የመንግስትና የህዝብን ሀብት ከምዝበራ ማዳን ነው ብለዋል፡፡ በብልሹ አሰራርና ባልተገቡ አሰራሮች ላይ እየተወሰደ ያለው ርምጃ የመንግሥትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እና በዜጎች ዘንድ ደግሞ መተማመንን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡   ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ትዕግስት ገብረየስ፤ መንግሥት ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚወስደው ርምጃ እስከታች ባለው የመንግሥት መዋቅር ገቢራዊ መደረግ አለበት ብለዋል፡፡ መንግሥት ተጠያቂነትን ለማስፈን የጀመረው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በማንሳት፤ ሂደቱ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ወጣት ቴዲ ዑለማ በበኩሉ፤ መንግሥት የህግ የበላይነትን ለማስፈን የተግባር ቁርጠኛ መሆኑን ያሳየ ርምጃ መሆኑን ተናግሯል፡፡   ሌላው አስተያየት ሰጪ አቢቲ ረጋሳ ሙስናና ብልሹ አሰራር የዕድገት ማነቆ መሆኑን በመግለጽ፤ ርምጃው አስተማሪና ትምህርት ሰጭ ነው ብለዋል፡፡   ማንም ሳይለፋና ሳይሰራ መበልጸግ የለበትም፤ ሙሰኞችን ለህግ ማቅረብ ተጠናክሮ መቀጠል ህዝቡም መተባበር አለበት ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በለጡ ዘላለም ናቸው፡፡      
አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ምህዳር ለመገንባት ወሳኝ የሆነውን ብቁ የሰው ሃይል የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Aug 11, 2026 49
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ምህዳር ለመገንባት ወሳኝ የሆነውን ብቁ የሰው ሃይል የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሂሚድ ገለጹ። 5ተኛው ዙር ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ የታዳጊዎች የስልጠና መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀምሯል።   መርሃ ግብሩ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሚያዘጋጀው ሲሆን በሳይበር ደህንነትና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ዝንባሌ ያላቸውን ታዳጊዎችና ወጣቶች ለማፍራት ያለመ ነው። የሳይበር ደህንነት፣ሶፍትዌር ልማት፣ኮዲንግ፣ አቪዬሽን፣የኤሮስፔስ ቴክኖሎጂ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች በመርሃ ግብሩ ተካተዋል። የሀርድ ዌር እና ሴኪዩሪቲ ዲዛይኖችን ማዘጋጀት የስልጠና መርሀ ግብር ሌላው የትኩረት ማዕከል ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤የኢትዮጵያን ዲጂታል ሽግግር ውጤታማ ለማድረግ የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው። ለዚህ ደግሞ በቁ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤አስተዳደሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሰው ሃይል የማፍራቱን ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል። የሰመር ካምፕ የስልጠና መርሃ ግብር የዚሁ አካል መሆኑን ጠቁመው፤ መርሃ ግብሩ የነገ የኢትዮጵያ ተስፋ የሆኑ ተተኪ ትውልድ በማፍራት ረገድ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። የስልጠና መርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ መጀመሩን አስታውሰው ፤ በአሁኑ ወቅት ስልጠናው በባህር ዳር፣ጅማ ፣ወላይታ ሶዶ፣ሀረማያ ዩንቨርስቲዎችን ጨምሮ በአስተዳደሩ ግቢ ውስጥ እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል።   የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ የቴክኖሎጂ አቅሙ የተገነባ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የጀመረው ተተኪ ትውልድ የማፍራት ስራ የሚያስመሰግን ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለመርሃ ግብሩ ስኬት ዩንቨርሲቲው የሚጠበቅበትን ድርሻ እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ሰልጣኞችም ኢትዮጵያን የማገልገል አደራ አለባቸሁ፤ለዚህ ደግሞ ስልጠናውን በአግባቡ ተከታትላችሁ ተገቢውን ክህሎት ልትጨብጡ ይገባል ብለዋል።
ወዳጅነት ፓርክ ፦ የመደመር እሴት ማሳያ
Aug 11, 2026 53
በሙሴ መለሰ በአዲስ አበባ መሐል የሚገኘው የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት ስምንት ዓመታት ከተገነቡት የመጀመሪያዎቹ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች አንዱ ነው። ይህ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውና 56 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ባለው የ“ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት” (Beautifying Sheger Project) ስር የተከናወነ ነው። ፕሮጀክቱ በሁለት ዋና ዋና ምዕራፎች ተከፍሎ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ሊጠናቀቅ ችሏል። ኢትዮጵያ የጀመረችው ይህ የከተማ ውበትና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ የውበት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ሀብት ፈጣሪ መሆኑንም በተግባር ያረጋገጠ ህያው ማሳያ ነው። የወዳጅነት አደባባይ የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሂደት በ2011 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን፣ ቀደም ሲል የቆሻሻ ማጠራቀሚያና ክፍት ቦታ የነበረውን ስፍራ ወደ ዘመናዊ አረንጓዴ ሥነ-ምህዳር ለመቀየር ያለመ ነበር። ግንባታው በ11 ወራት ብቻ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ በጳጉሜ 2012 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በቀድሞዋ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት ሆኗል። ይህ ክፍል 32 ሄክታር መሬት በማልማት፣ አሳ እና ዳክዬዎች የሚቀዝፉበት ሰው ሠራሽ ሐይቅ፣ ትልቅ አደባባይ (Square)፣ እና 1 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻን መልሶ ማቋቋምን ያካተተ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ለምሽት መዝናኛ የሚሆን ማራኪ የፏፏቴ ላይ የብርሃን ትርኢት (Dancing Fountain)፣ ከ16 በላይ የውጪ ላይ ስብሰባ ማካሄጃ ቦታዎች (Event Venues)፣ የሰርግ አፀዶች፣ ካፌዎች፣ የፎቶ ስቱዲዮዎች እና ጠዋት ጠዋት የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ሩጫ ለማድረግ ምቹ የሆኑ የተከለሉ መንገዶችን ይዟል። ምዕራፍ አንድ ከተመረቀ በኋላ ወዲያውኑ የሁለተኛው ምዕራፍ (Friendship Park 2) የዲዛይንና የዝግጅት ሥራዎች ተጀምረዋል። በግንባታው ወቅት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም፣ ከሌላ ቦታ የተሰባሰቡ ከ4ሺህ በላይ አገር በቀል ትልልቅ ዛፎች (Indigenous trees) መጥተው በቦታው ላይ በተሳካ ሁኔታ እንዲተከሉ ተደርጓል። ግንባታው በጥቅምት 2015 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተመርቋል። 16 ሄክታር መሬት የሸፈነው ይህ ክፍል ከአብርሆት ቤተ-መጽሐፍት ፊት ለፊት የሚገኝ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ለሕፃናት፣ ለታዳጊዎችና ለቤተሰብ ስፖርታዊ መስተጋብር ተለይቶ የተገነባ ነው። በውስጡም እጅግ ዘመናዊና ሰፊ የሕፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን (Playgrounds)፣ ታዳጊዎች እየተጫወቱ ሳይንስና ቴክኖሎጂን የሚለማመዱበትን የሳይንስ ማዕከል፣ ትንንሽ የእግር ኳስ (Mini-football) እና የቅርጫት ኳስ (Basketball) ሜዳዎችን፣ የሩጫ ትራኮችን፣ ለወጣቶች ንባብ የሚሆኑ ቦታዎችን (Reading nooks) እና ከጎኑ ያለውን የሳይንስ ሙዚየም ግንባታን ያካተተ ሰፊ ይዘት አለው። የወዳጅነት ፓርክ ከብሔራዊ ቤተመንግሥት እስከ መስቀል አደባባይባለው አካባቢ የሚዘልቅ ዘመናዊ የሕዝብ መገልገያና መዝናኛ ማዕከል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፣ ይህ ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ ማስገኘት ችሏል። ይህም የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ራሳቸውን ችለው ከፍተኛ ገቢ ማመንጨት ከመቻል ባለፈ፣ በቱሪዝም ዘርፉ፣ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዘንድ ለበርካታ ዜጎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሰፊ የሥራ ዕድል እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እየፈጠረ ይገኛል። ከዚህ ኢኮኖሚያዊ እሴቱ ባሻገር፣ ፕሮጀክቱ የከተማ ነዋሪዎችን ማኅበራዊ ትስስር በከፍተኛ ደረጃ ያጠናክራል፤ የዜጎችን የኑሮ ጥራት፣ የጤና ሁናቴ እና ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ (Life style) ከማሻሻል አንጻርም የመደመር እሴት በተግባር መሬት ማወረዱንና የዜጎችን አገራዊ የባለቤትነት ስሜት በጽኑ የሚያሳድግ ትልቅ ማሳያ ነው። ፓርኩ ለጤና፣ ለአካል ብቃት፣ ለመዝናኛና ለንባብ ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ወጣቶች ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን በስፖርት፣ በዕውቀት ቀሰማና በሌሎች በጎ ነገሮች ላይ እንዲያሳልፉ ምቹ ከባቢ ፈጥሯል። በተጨማሪም ቦታው ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎችና ጎብኝዎች በየቀኑ በስፋት የሚገናኙበት ማዕከል መሆን ችሏል። በስፍራው ከቤተሰቦችና ሕፃናት፣ ከስፖርት ቡድኖችና ከሠርግ ተካፋዮች ጀምሮ እስከ ዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎች በከፍተኛ ቁጥር ይገኙበታል። ይህም ለሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች (Content Creators) ምቹ ከባቢ በመፍጠር፣ የአዲስ አበባን ዘመናዊና ማራኪ ገጽታ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ በስፋት እንዲያስተዋውቁና የከተማዋን በጎ ስም ለዓለም እንዲያደርሱ ትልቅ ዕድል ከፍቷል። ይህ ፓርክ አዲስ አበባን ለሌሎች የክልል ከተሞች በአረንጓዴ ልማት፣ በጽዳትና በዘመናዊ የሕዝብ መገልገያዎች በሞዴልነት የሚጠቀስ ሲሆን፣ የከተማዋን የዲፕሎማሲያዊ መዲናነት ገጽታ ይበልጥ በማደስ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች፣ ለዲፕሎማቶችና ለዓለም አቀፍ እንግዶች በጣም ሳቢና ተመራጭ መዳረሻ አድርጓታል። ፓርኩ በከተማዋ እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ውስጥ እየተገነቡ ላሉ ተመሳሳይ የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ቀዳሚ ማሳያ ሲሆን፣ እነዚህ አዳዲስ ቦታዎች እሴት የሚፈጥሩ፣ ዕድሎችን የሚያመቻቹ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያንን ባለቤትነት የሚያረጋግጡ ማዕከላት መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ያረጋግጣል።
የሚታይ
አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ምህዳር ለመገንባት ወሳኝ የሆነውን ብቁ የሰው ሃይል የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Aug 11, 2026 49
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ምህዳር ለመገንባት ወሳኝ የሆነውን ብቁ የሰው ሃይል የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሂሚድ ገለጹ። 5ተኛው ዙር ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ የታዳጊዎች የስልጠና መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀምሯል።   መርሃ ግብሩ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሚያዘጋጀው ሲሆን በሳይበር ደህንነትና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ዝንባሌ ያላቸውን ታዳጊዎችና ወጣቶች ለማፍራት ያለመ ነው። የሳይበር ደህንነት፣ሶፍትዌር ልማት፣ኮዲንግ፣ አቪዬሽን፣የኤሮስፔስ ቴክኖሎጂ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች በመርሃ ግብሩ ተካተዋል። የሀርድ ዌር እና ሴኪዩሪቲ ዲዛይኖችን ማዘጋጀት የስልጠና መርሀ ግብር ሌላው የትኩረት ማዕከል ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤የኢትዮጵያን ዲጂታል ሽግግር ውጤታማ ለማድረግ የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው። ለዚህ ደግሞ በቁ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤አስተዳደሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሰው ሃይል የማፍራቱን ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል። የሰመር ካምፕ የስልጠና መርሃ ግብር የዚሁ አካል መሆኑን ጠቁመው፤ መርሃ ግብሩ የነገ የኢትዮጵያ ተስፋ የሆኑ ተተኪ ትውልድ በማፍራት ረገድ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። የስልጠና መርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ መጀመሩን አስታውሰው ፤ በአሁኑ ወቅት ስልጠናው በባህር ዳር፣ጅማ ፣ወላይታ ሶዶ፣ሀረማያ ዩንቨርስቲዎችን ጨምሮ በአስተዳደሩ ግቢ ውስጥ እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል።   የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ የቴክኖሎጂ አቅሙ የተገነባ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የጀመረው ተተኪ ትውልድ የማፍራት ስራ የሚያስመሰግን ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለመርሃ ግብሩ ስኬት ዩንቨርሲቲው የሚጠበቅበትን ድርሻ እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ሰልጣኞችም ኢትዮጵያን የማገልገል አደራ አለባቸሁ፤ለዚህ ደግሞ ስልጠናውን በአግባቡ ተከታትላችሁ ተገቢውን ክህሎት ልትጨብጡ ይገባል ብለዋል።
በአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የተጀመሩ ውጤታማ የለውጥ ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Aug 11, 2026 81
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የተጀመሩ ውጤታማ የለውጥ ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ዓለምአንተ አግደው ገለፁ። የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ክንውን እና የ2019 የትኩረት አቅጣጫዎች የውይይት መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተጀምሯል። ፕሬዝዳንቱ አቶ ዓለምአንተ አግደው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ የፍርድ ቤቶችን አሰራር በቴክኖሎጂ ታግዞ በማዘመን በኩል ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።   በተለይ ቀደም ሲል ማህበረሰቡ በአሰራር ዙሪያ ያነሳቸው የነበሩ ቅሬታዎችንና አቤቱታዎችን በዘላቂነት ለመፍታት ባለፋት ሦስት ዓመታት የፍርድ ቤቶች የትራንስፎርሜሽን እቅድ ተግባራዊ መደረጉን አስታውሰዋል። በተቀናጀ አግባብ በተሰሩ የለውጥ የአሰራር ማሻሻያዎች፣ የዲጅታላይዜሽን ትግበራዎች እና የተቋማት ግንባታዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልፀዋል። በዚህም በፍርድ ቤቶች በሚታዩ መዝገቦች ቁጥር፣ የዳኝነት አሰጣጥ ጥራትና ፍጥነት ከፍተኛ መሻሻል መታየቱን አረጋግጠዋል። መደበኛ ፍርድ ቤቶች ግልፅና ተጠያቂነት ባለው መንገድ መዳኘት ያስቻለ የቴክኖሎጂ አሰራር ተግባራዊ በማድረግ ማዘመን እንደተቻለም ተናግረዋል። እንዲሁም አማራጭ የዳኝነት መስጫ ማዕከላትን ተደራሽ በማድረግም ዜጎች በአቅራቢያቸው ሆነው ያለምንም ወጭና ድካም የዳኝነት አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም አሰገንዝበዋል። ፍርድ ቤቶች ገለልተኝነትና ነፃነታቸውን በጠበቀ መንገድ ከተቋማት ጋር በጠንካራ ትብብርና ቅንጅት እየሰሩ እንደሆነም አስገንዝበዋል። የዳኝነትና የፍትህ አሰጣጡን በማዘመንና ተደራሽነታቸውን በማሳደግ ማህበረሰቡ የበለጠ የሚተማመንባቸው በማድረግ በኩል የተጀመሩ የለውጥና የዲጂታላይዜሽን ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል። በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ዙሪያ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል፤ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡም እውቅናም እንደሚሰጥ ነው የተገለፀው። የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን የለውጥ ስራ እና የዲጅታላይዜሽን ትግበራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባለፈው ሳምንት መጎብኘታቸው ይታወሳል።  
በሐረሪ ክልል ለኢንዱስትሪው ዘርፍ የተደረጉ ድጋፎች ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል
Aug 11, 2026 225
ሐረር ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ) ፡-በሐረሪ ክልል የኢንዱስትሪውን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ለማጉላት የተደረጉ ድጋፎች ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገባቸውን የክልሉ ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ እስማኤል ዩሱፍ ገለፁ። በክልሉ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ የተሰጠው ትኩረት የሥራ እድል ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ወጣቶች ተናግረዋል።   የክልሉ ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ እስማኤል ዩሱፍ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት፤ በክልሉ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ የተሰጠው ትኩረት 231 አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲገቡ አድርጓል። የኢንዱስትሪ ዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግም የመሠረተ ልማት አቅርቦት፣ ድጋፍና ክትትል መጠናከሩን ተናግረዋል።   ይህም የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም በማሳደግ፣ ከ49 ሺህ ቶን በላይ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት 60 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል። የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ማደግ ለዜጎች የሥራ ዕድል እንዲፈጠር ማስቻሉንም ተናግረዋል። በቀጣይም አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በተለይ የኮንስትራክሽን፣ የምግብና መጠጥ፣ የቆዳና የቆዳ ውጤቶችና ሌሎች ዘርፎችን የማስፋፋትና የማዘመን ሥራ በትኩረት ይከናወናል ብለዋል።   በክልሉ በተደረገላቸው ድጋፍ ውጤታማ ከሆኑ ኢንዱስትሪዎች መካከል የታቲ የከረጢትና ጫማ ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዑመር መሐመድ እንዳሉት፤ ፋብሪካው ፌስታልን ከማምረት ወጥቶ ተኪ የሆኑ የከረጢትና የጫማ ምርቶችን ማምረት መጀመሩን ተናግረዋል። ይህም የማምረት አቅሙን በማሳደግ በገበያ ተወዳዳሪ ከመሆን አልፎ፣ ለአገር እድገት ያለውን አበርክቶ በማሳደግ ለዜጎች የሥራ እድል መፍጠሩን ጠቁመዋል።   በክልሉ የአምራች ኢንዱስትሪ መስፋፋትን ተከትሎ በተፈጠረለት የሥራ እድል ተጠቃሚ በመሆኑ ራሱንና ቤተሰቡን ከመደገፍ ባለፈ የቴክኖሎጂ ክህሎቱን እያዳበረ መሆኑን የተናገረው ደግሞ ወጣት መሐመድ ዙቤር ነው። በክልሉ ኢንዱስትሪ ዞን በአልባሳት ማምረት ላይ በተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች የሥራ እድል ከተፈጠረላቸው መካከል ጽዮን ሻውል በበኩሏ፤ የተገኘው የሥራ እድል ቤተሰቧን ለማስተዳደር እንዳገዛት ተናግራለች።  
የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ አስገኝቷል
Aug 11, 2026 157
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ መሐል የሚገኘው የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ አስገኝቷል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት ስምንት ዓመታት በመደመር መንግሥት ከተገነቡት የመጀመሪያዎቹ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች አንዱ ነው ብለዋል። በዚህም ይህ ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ ያስገኘ ሲሆን፣ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሥራ ዕድሎችንና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ፈጥሯል ነው ያሉት። ከሁሉም በላይ ደግሞ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎችና ጎብኝዎች የሚገናኙበት ሥፍራ መሆን ችሏል።   ከቤተሰቦችና ሕፃናት፣ከስፖርት ቡድኖችና ከሠርግ ተካፋዮች ጀምሮ እስከ ዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎች በቦታው ይገኙበታል። የወዳጅነት ፓርክ ከኢኮኖሚያዊ እሴቱ ባሻገር ለጤና፣ ለአካል ብቃት፣ ለመዝናኛና ለሕብረተሰብ ትስስር ትልቅ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። ይህም በጥሩ ሁኔታ የታቀዱ የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ለአዲስ አበባ ከተማ አጠቃላይ የከተማነት ዕድገት አስተዋጽኦ እያበረከቱ ሰዎችን እንዴት ማገናኘት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ነው ያሉት።   ይህ ፓርክ በከተማዋ እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ውስጥ እየተገነቡ ላሉ ተመሳሳይ የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ቀዳሚ ማሳያ እንደሆነም ገልጸዋል። እነዚህ አዳዲስ ቦታዎች እሴት የሚፈጥሩ፣ ዕድሎችን የሚያመቻቹ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያንን ባለቤትነትን የሚያረጋግጡ ማዕከላት መሆናቸውን ነው የገለጹት።
መሶብ የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ልምድ ለአፍሪካ ሀገራትም ያግዛል
Aug 10, 2026 681
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ልምድ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ከፍተኛ ተሞክሮ የሚወስዱበት መሆኑን የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ ገለጹ። የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትን ጎብኝተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚው ለጎብኚዎች በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት የኢትዮጵያ የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ልምድ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመንግሥት አገልግሎት ሥርዓትን እንዲገነቡ ያግዛል።   የመንግሥት አገልግሎቶች በተለያዩ ተቋማት ተበታትነው መሰጠታቸው ዜጎች ለአገልግሎት ብዙ ተቋማት ጋር እንዲሄዱ ከሚያደርጉ ችግሮች ዋነኛው ነበር ብለዋል። ይህን ችግር ለመፍታት መሶብ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትንና አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በማቀናጀት የአንድ መስኮት አገልግሎት አሰጣጥን በተግባር እያስፋፋ መሆኑን ገልጸዋል። የመሶብ አገልግሎት ከአንድ ማዕከል አገልግሎት በመነሳት ወደ ተንቀሳቃሽና የቤት ለቤት አገልግሎት እንዲሁም ወደ ዲጂታል መድረክ መስፋፋቱንም አስረድተዋል። በተለይም “ዩኒፋይድ መሶብ” የተሰኘው የኦንላይን መድረክ ዜጎች በሞባይል ስልካቸው የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችል ሥርዓት መሆኑን ገልጸዋል።   በተጨማሪም የመሶብ የዲጂታል አገልግሎት ልምድን ከኢትዮጵያ ውጭ ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። በቀጣይ ከጅቡቲ፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከኬንያና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር በዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት ዙሪያ ትስስር በመፍጠር የአህጉራዊ ዲጂታል ሥርዓት መገንባት የመሶብ ራዕይ እንደሆነ ገልጸዋል። በዘርፉ የኢትዮጵያን ልምድ ለአፍሪካ ሀገራት ማካፈል የሚያስችል መድረክ ለመሆን እየሰራ መሆኑም ተገልጿል። የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች በፌዴራል መሶብ ዋና ማዕከል የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የምክክር ጉባኤው በሀሳብ ብዝሃነት የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ተስፋ ሰጪ ነው- ተመካካሪዎች
Aug 11, 2026 42
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5 /2018(ኢዜአ)፦የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን እያሳተፈ የሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ፣ የሀሳብ ብዝሃነትን በማንጸባረቅ ለጋራ መግባባትና ለዘላቂ ሰላም መሠረት የሚጥል ተስፋ ሰጪ ሂደት መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች እንደተናገሩት፤ ምክክሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ ማህበረሰቦች እኩል ሀሳባቸውን እንዲያቀርቡ ዕድል በመስጠት አካታችነቱን እያረጋገጠ ነው። ከተመካካሪዎቹ መካከል አባገዳ ለሜቻ ለማ እንደገለጹት፤ በምክክሩ ላይ የተለያዩ ሀሳቦች በነፃነት እየቀረቡና እየዳበሩ ይገኛሉ። በምክክሩ ሁሉም ተመካካሪ ሀሳቡን በነጻነት እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ይህም በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን ደረጃ በደረጃ መፍታት የሚያስችል የመፍትሔ ሀሳብ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የጋራ መግባባት የተፈጠረባትና አንድነቷ የጸናች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል።   ሌላው ተመካካሪ ባዬ በሬ በበኩላቸው፤ ምክክሩ ከአካታችነት አንጻር ሁሉንም የሚያሳትፍና የሀሳብ ብዝሃነት የሚንጸባረቅበት መሆኑን ገልጸዋል። በምክክሩ ላይ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ሀሳቦች እየቀረቡ መሆናቸውን ገልፀው ፤ ይህም የተሻለ ነገን መገንባት እንደሚቻል እየታየ መሆኑን ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል በሚወክል መልኩ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አለሙ አሻግሬ (ዶ/ር) ናቸው።   ሀገራዊ ምክክሩ ችግሮችን በምክክር የመፍታት አዲስ ባህል መሆኑን ገልጸው፤ ሂደቱ ዛሬ ላይ ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ የምትሆን የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት እንደሚያስችል ጠቁመዋል።  
የምክክር ጉባኤው የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክር ነው-የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
Aug 11, 2026 94
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክርና ኢኮኖሚ ዕድገትን ለማፋጠን የሚያስችል የጋራ መግባባት ይገነባል የሚል ተስፋ አለን ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በጉባኤውም በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች፣በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፣ የምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያውያን መካከል የጋራ መግባባትን በመፍጠር ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ወሳኝ መንገድ እንደሆነ ከፍተኛ እምነት አላቸው። የምክክር ሂደቱ የሀገርን አንድነት ለማጠናከር፣ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማሳደግ የሚያስችል የጋራ መግባባት እንደሚፈጥር ትልቅ ተስፋ የጣሉበት መሆኑንም ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ሮቤል ብርሃኑ፣ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን የሚገነባ አዋጭና ስልጡን አካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። በሀገራዊ ችግሮች ዙሪያ በአንድ ጣሪያ ሥር ምክክር ሲደረግ፣በመሠረታዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባትን ለመገንባት የሚያስችል ወሳኝ መንገድ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በፖለቲካው መስክ መግባባትን በመፍጠር የሀገርን የኢኮኖሚ አቅም የሚገነባ የተረጋጋ የልማት ሥራን ለማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤም የኢኮኖሚ ዕድገትና የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክር የጋራ መግባባት የሚገነባ አዎንታዊ ምክረ ሐሳቦች የሚፈልቁበት እንደሚሆን ተስፋ አለኝ ብለዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ኃይሌ ዓለማየሁ በበኩላቸው፣ የአንድ ሀገር ዜጎች በጋራ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የምክክር ሐሳብ በመወጠን መሰባሰባቸው በራሱ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል። ከዚህ ታሪካዊ መድረክ በኋላም የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያሳልጥ የጋራ መግባባትን በመገንባት፣ኢትዮጵያ በአፍሪካ ደረጃ መሪ ሀገር ለመሆን የሚያስችላትን አቅም እንደምትፈጥር እምነታቸውን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው አካታችነት በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን በመገንባት የሕዝብ አንድነትን ይበልጥ ያጠናክራል የሚል ተስፋ አለኝ ያሉት ደግሞ ያደታ ጉደታ ናቸው። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ አልማዝ ታምራት በበኩላቸው፣ የምክክር ጉባኤው በዜጎች መካከል ጠንካራ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት መሠረት የሚጥል የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የመዲናዋ ነዋሪ አስቻለው በርጋ እንዲሁ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመፍጠር የሚያግዝ ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል። አቶ ገረመው ደበበ በበኩላቸው፣ የሀገራዊ ምክክሩ ውጤትም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘላቂ ሰላምና የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን የጋራ መግባባት ይፈጥራል የሚል እምነት አለኝ ብለዋል።
ኢትዮጵያን ማስቀደም፡ሀገራዊ ምክክሩና የዜጎች ዘላቂ መግባባት የመፍጠር ቁርጠኝነት
Aug 11, 2026 197
ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ በመመካከር ዘላቂ መግባባት ላይ ለመድረስ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያሳየው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በዜጎች የነቃ ተሳትፎ መካሄዱን ቀጥሏል። ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው ይህ ታሪካዊ ጉባኤ፣ በኢትዮጵያ ዘመናት የተሻገሩ ውስብስብ ችግሮችንና ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት የመፍታት አዲስ ባህል እየገነባ ይገኛል። ተመካካሪዎች በስምንት አጀንዳዎች በመካከር ላይ ይገኛሉ። አጀንዳዎቹ የተለዩት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ካደረገ በኋላ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የቀረቡት ስምንቱ አጀንዳዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ ድምፅ፣ ቅሬታ፣ ፍላጎት፣ ተስፋና ስጋት የተቀዱ መሆናቸውን ኮሚሽኑ አመልክቷል።   ኮሚሽኑ በማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 በተሰጠው ስልጣን መሰረት፣ የህዝብን ቀጥተኛ ተሳትፎ ያረጋገጠና "ከታች ወደ ላይ" የሚለውን ስልት የተከተለ አካታችና ሁሉን አቀፍ ስራ ማከናወኑን አስታውቀዋል። የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር እንዲሁም ሰላም ግንባታ ምክክር እየተደረገባቸው ያሉ አጀንዳዎች ናቸው። የሕዝቦችን አሰባሳቢ እሴቶች ለማጠናከርና የተራራቁ ትርክቶችን ወደ አንድነት ለማምጣት ያለመው ይህ የምክክር ሂደት፣በአሁኑ ወቅት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ከነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከስልታዊ ቡድኖች የቀረቡ የአጀንዳ ምክረ-ሃሳቦች ተቀናጅተው ለስራ ቡድኖች መቅረብ የጀመሩ ሲሆን፣ምክረ ሀሳቦቹን የማቅረብ ሂደት ዛሬም ቀጥሎ እየተካሄደ ይገኛል። በዚህም በተጠናቀሩት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ያተኮረ ሰፊ ውይይት ቀጥሎ በመካሄድ ላይ ነው። በእያንዳንዱ 500 አባላት ባሉት 8 የስራ ቡድኖች ውስጥ ከተመረጡ 30 ተወካዮች የቀረቡት እነዚህ ሃሳቦች፣ ወደ አካታችና የመጨረሻ ምክረ-ሃሳብነት እንዲያድጉ በጥልቀት እየመረመሩ ይገኛሉ። በጉባኤው ላይ 4000 በቀጥታ የሚሳተፉ ተመካካሪዎች የተገኙ ሲሆን፣ እነዚህም በስምንት ተመካካሪ ቡድኖች ተከፋፍለው በስምንት ቁልፍ የምክክር አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት በመወያየት ላይ ይገኛሉ። ሂደቱን በስልትና በስርዓት ለመምራት 16 ስልታዊ ቡድኖች፣160 አመካካሪዎች፣ 158 ቃለ-ጉባኤ ያዦች እንዲሁም የሙያ ድጋፍ የሚሰጡ 80 የባለሙያዎች ቡድን (Panel of Experts) ተመድበው በቅንጅት እየሰሩ ነው። በተጨማሪም የሁሉንም ወገን ድምፅ ለማካተት ሲባል 336 የክልልና የፌዴራል ተወካዮች በሂደቱ ላይ በነቃ ሁኔታ በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል። ይህ ምክክር ዜጎች ከግል፣ከቡድን ወይም ከአካባቢያዊ እሳቤዎች ሙሉ በሙሉ በመውጣት ኢትዮጵያን በማስቀደም እየተካሄደ ይገኛል። ሕብረተሰቡ በየደረጃው የሚያደርገው የነቃ፣ግልጽና አካታች ተሳትፎ፣በኢትዮጵያ የጋራ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ባህልን ከማሳደጉም በላይ የዜጎችን እውነተኛ ባለቤትነት ያረጋገጠ ነው። ይህ ሀገራዊ ምክክር ለሀገር ዘላቂ ሰላም፣ወንድማማችነትና የጋራ ዕድገት ጽኑ መሰረት የሚጥል ታሪካዊ ክስተት ነው። ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሙሉ ነፃነትና ተስፋ ተወያይተው የጋራ መግባባት በመፍጠር፣ ሀገራቸውን ወደ ተሻለ የልማትና የስልጣኔ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችላቸውን አዲስ ተስፋ በጋራ በመገንባት ላይ ይገኛሉ።
የምክክር ጉባኤው ሂደት ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው
Aug 10, 2026 789
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደት ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ፡፡ የምክክሩ አካሄድ የውሳኔ የመስጠት ሂደት ሳይሆን ምክረ ሀሳብ ማቅረብ መሆኑንም አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ የምክክር ሂደቱን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ በሰጡት መግለጫ፣ የምክክር ሂደቱ እየተጠናከረና ወደ ተሻለ ደረጃ እየተሸጋገረ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ከዚህ ቀደም ከ10 እና ከ50 ተሳታፊዎች ተነስተው የነበሩ ሀሳቦች ወደ 250 ቡድኖች ማደጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡ አሁን ባለው ደረጃ ሁለቱ የ250 ቡድኖች የተነጋገሩባቸውንና የሰሯቸውን ስራዎች አጠናቅረውና ሰንደው ለ500ዎቹ ቡድኖች ማቅረብ መጀመራቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የቀጣዩን ምዕራፍ የጀመሩ የ500 ቡድን አባላት የቀረቡላቸውን ሀሳቦች በማዳመጥ፣መካተት ያለባቸውንና የሚገባቸውን ሀሳቦች በደንብ እያዳበሩ ይገኛሉ ብለዋል። እስካሁን 250 ሆነው በመወያየት ላይ የሚገኙ ተመካካሪዎች ዛሬ ከሰዓት በኋላ የሚጨርሱ እና ነገ ጠዋትም የሚጨርሱት ደግሞ ነገ ከሰአት በኋላ ለ500 ቡድኖቻቸው የሚያቀርቡ ይሆናል ብለዋል። በሂደቱ መጀመሪያ ላይ የተለያዩ አስተያየቶች፣ ክርክሮች እና የተለያዩ ስሜት መንጸባረቆች መታየታቸው የምክክሩን አሳታፊነት እና ህያውነት የሚያሳዩ ተፈጥሮአዊ የውይይት ማሳያዎች መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ የተለያዩ ሀሳብ የመስጠት ፍላጎቱ የሚመጣው ተሳታፊዎች የየራሳቸውንና የረጅም ጊዜ ጥያቄዎቻቸውን ለማንጸባረቅ ትክክለኛው አጋጣሚ ነው ብለው ስለሚያምኑ ነው ብለዋል። አልፎ አልፎ የሚታዩ ስሜታዊነት በምክክር ኮሚሽኑ የስብሰባ ስነ-ስርዓት ደንብ በጭራሽ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። በምክክር ሂደቱ ውስጥ አንደኛው መርህ መከባበር ሲሆን፣ ሁለተኛው መነጋገር፣ መደማመጥና ወደ መሀል መምጣት በመሆኑን ተመካካሪዎች ይህንን ሊያጠናክሩ ይገባል ብለዋል። ተሳታፊዎች የመጡት በየመንደሩና በየአካባቢው ያለውን ጥያቄ እዚያው እንዲመለስ ለማድረግ ሳይሆን ኢትዮጵያን ማዕከል አድርገው መመካከር እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡ የምክክሩ አካሄድ የውሳኔ የመስጠት ሂደት ሳይሆን ምክር ሀሳብ ማቅረብ መሆኑን ጠቁመው፤ ምክረ ሀሳቦቹ ለህግ አስፈጻሚው፣ ለህግ አስከባሪው፣ ለህግ አውጪው፣ ለህግ ተርጓሚው፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎችና ለሲቪል ማህበራት የሚተላለፉ ናቸው ብለዋል። "በድምፅ ብልጫ ውሳኔ ይሰጣል" ወይም "ከውስጥና ከውጭ ጫና ተደርጎ ውሳኔ ሊያስተላልፉ ነው" የሚባለው ወሬ ከአሉባልታ ያለፈ አይደለም ብለዋል። በአሁኑ ሰዓት በተመካካሪዎች መካካል የሚታዩ ክርክሮችና አለመግባባት በ"ዳይቨርጀንስ" (የመበታተን) ምዕራፍ ላይ ያለ በመሆኑ አግባብነት ያለውና ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል። ወደ መሰብሰብ ምዕራፍ (ኮንቨርጀንስ) ስንመጣ የራሳችንን የግል ሀሳብ እየጣልን ኢትዮጵያን ማዕከል ያደረገ የጋራ ሀሳብ ይዘን እንሄዳለን ብለዋል። በጣም ያጨቃጭቃሉ ተብለው የነበሩ አጀንዳዎች ቀደም ብለው ህዝቡ "የጋራችን ነው" በማለት ወደ መሀል ያመጣቸው ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል። ምክክሩ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው ከአንድ ወር ልፋት በኋላ በሚቀጥሉት አንድ እና ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከ4ሺህ ተሳታፊዎች ጋር ያለው የምክክር ሂደት ይገባደዳል ብለዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ኮሚሽኑ የመጡት ሀሳቦች አጠናክሮ ለተግባራዊው አካል የሚላኩ ሲሆን፣ መተግበራቸውም እየተከታተለ ለህዝብ ይፋ ይደረጋል ብለዋል። ዋና ኮሚሽነሩ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ሆነው ሂደቱን በትህትና ለሚከታተሉ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
​​​​​​​በምክክር ጉባኤው የሚተላለፍ ውሳኔ የለም - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ
Aug 10, 2026 738
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የሚተላለፍ ውሳኔ እንደሌለና ዋና ዓላማው ለተግባራዊ አካላት ምክረ ሀሳቦችን ማዘጋጀት መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። ከ10ሩ ቡድኖች የተውጣጡ ሁለቱ የ250 አባላት ስብስብ ያዘጋጁትን ሃሳብ በጋራ እያጠናቀሩ እንደሚገኝ ዋና ኮሚሽነሩ አመልክተዋል። በመቀጠልም እነዚህ ሁለቱ የ250 ቡድኖች በጋራ በመሆን ለ500 አባላት የተወያዩባቸውን ሀሳቦች ለ500ዎቹ እያቀረቡ እንደሚገኝና ይህ ሂደት ቀጣይነት እንዳለው ጠቁመዋል። ባለ 500ዎቹ የአጀንዳ ቡድኖች በሃሳቦቹ ላይ አስተያያት በመስጠት አጀንዳዎቹ እንዲዳብሩ እያደረጉ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በአሁኑ ሰዓት የ500 ምክክር መጀመሩንና ሁሉም የ500 ተመካካሪ ቡድኖች በሁለት ቀናት ሙሉ ለሙሉ ወደ ምክክር እንደሚገቡም ጠቁመዋል። ከተለያዩ ማህበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ተመካካሪዎች የተለያዩ ሀሳቦችና ጥያቄዎችን በማንሳት እየመከሩ እንደሚገኝና አጠቃላይ ሂደቱ ጥሩ የሚባል እንደሆነ አንስተዋል። በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የሚወሰን ውሳኔ የለም ያሉት ዋና ኮሚሽኑ የሂደቱ ዋና አላማ ምክረ ሀሳቦችን ማቅረብ ነው ብለዋል። በጉባኤው የሚቀርቡ ምክር ሀሳቦች መንግስት እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ጨምሮ በተግባሪ አካላት እንደሚፈጸሙ አስገንዝበዋል። በምክክሩ ላይ እንደዚህ አይነት ውሳኔዎች ሊተላለፉ ነው የሚሉ ሀሳቦች ከአሉባልታ የዘለለ ትርጉም እንደሌላቸው ተናግረዋል። የምክክር ጉባኤው አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ የተለያዩ የማይስማሙ ሀሳቦች መነሳታቸው አግባብና ተፈጥሯዊ ሂደት መሆኑን ጠቅሰው ይህም በቀጣይ ሀሳብን ወደ መሐል ለማምጣት ሂደት ወሳኝ መሰረት እንደሚጥል ነው ያነሱት። የመሰባሰብ ምዕራፍ ላይ ሲደርስ የግል ሀሳቦች እየተጣሉ ኢትዮጵያን ያማካሉ የጋራ ሀሳቦች እንደሚመጡም አንስተዋል። በስምንቱ አጀንዳዎች ላይ የሚደረጉ ውይይቶች በቀጣይ የተሻለ ምክረ ሀሳቦች እንደሚገኝባቸው ዋና ኮሚሽነሩ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ እየተካሄደ ይገኛል።
በሃገራዊ ምክክሩ ባለ 500 ተመካካሪ ቡድኖች የቀረቡላቸውን ሃሳቦች እያዳበሩ ይገኛሉ - መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)
Aug 10, 2026 682
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ባለ 500 ተመካካሪ ቡድኖች 250 አባላት ባሏቸው ስልታዊ ቡድኖች የቀረቡላቸውን ሃሳቦች እያዳበሩ እንደሚገኙ የሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ገለጹ፡፡ ዋና ኮሚሽነሩ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን አሁናዊ ሂደት አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ። ከነሃሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከስምንቱም ቡድኖች በተመረጡ 30 አባላት ከስልታዊ ቡድኖች የቀረቡ የአጀንዳ ምክረ ሃሳቦችን ተቀናጅተው 500 አባላት ላሏቸው 8 የስራ ቡድኖች መቅረብ መጀመራቸውን ጠቁመዋል። ይህ የምክክር ደረጃ 500 ተመካካሪዎች በሚወያዩበት አጀንዳ ላይ የመጨረሻ ምክረ ሀሳብ ለማቅረብ ጥልቅ ውይይት የሚያደርጉበት መሆኑንም ገልጸዋል። በእነዚህ የተጠናቀሩ የአጀንዳ ሃሳቦች ላይ የመወያየቱ ሂደት እስከ ዛሬ ድረስ የቀጠለ መሆኑን ገልጸው 500 አባላት ላሏቸው 8 የስራ ቡድኖች የቀረቡ ሃሳቦችን እያደበሩ ይገኛሉ ብለዋል። በስልታዊ ቡድኖቹ የቀረቡላቸውን አጀንዳዎች አዳብረው የጨረሱ እንዳሉ ሁሉ ያላጠናቀቁ ቡድኖችም በሚጨርሱበት ጊዜ ቀጣዩ ቡድን እንደሚያስረክቡ ተናግረዋል።
ፖለቲካ
የምክክር ጉባኤው በሀሳብ ብዝሃነት የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ተስፋ ሰጪ ነው- ተመካካሪዎች
Aug 11, 2026 42
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5 /2018(ኢዜአ)፦የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን እያሳተፈ የሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ፣ የሀሳብ ብዝሃነትን በማንጸባረቅ ለጋራ መግባባትና ለዘላቂ ሰላም መሠረት የሚጥል ተስፋ ሰጪ ሂደት መሆኑን ተመካካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች እንደተናገሩት፤ ምክክሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ ማህበረሰቦች እኩል ሀሳባቸውን እንዲያቀርቡ ዕድል በመስጠት አካታችነቱን እያረጋገጠ ነው። ከተመካካሪዎቹ መካከል አባገዳ ለሜቻ ለማ እንደገለጹት፤ በምክክሩ ላይ የተለያዩ ሀሳቦች በነፃነት እየቀረቡና እየዳበሩ ይገኛሉ። በምክክሩ ሁሉም ተመካካሪ ሀሳቡን በነጻነት እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ይህም በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮችን ደረጃ በደረጃ መፍታት የሚያስችል የመፍትሔ ሀሳብ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የጋራ መግባባት የተፈጠረባትና አንድነቷ የጸናች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልጸዋል።   ሌላው ተመካካሪ ባዬ በሬ በበኩላቸው፤ ምክክሩ ከአካታችነት አንጻር ሁሉንም የሚያሳትፍና የሀሳብ ብዝሃነት የሚንጸባረቅበት መሆኑን ገልጸዋል። በምክክሩ ላይ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ሀሳቦች እየቀረቡ መሆናቸውን ገልፀው ፤ ይህም የተሻለ ነገን መገንባት እንደሚቻል እየታየ መሆኑን ተናግረዋል። የምክክር ሂደቱ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል በሚወክል መልኩ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ተመካካሪ አለሙ አሻግሬ (ዶ/ር) ናቸው።   ሀገራዊ ምክክሩ ችግሮችን በምክክር የመፍታት አዲስ ባህል መሆኑን ገልጸው፤ ሂደቱ ዛሬ ላይ ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ የምትሆን የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት እንደሚያስችል ጠቁመዋል።  
የምክክር ጉባኤው የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክር ነው-የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
Aug 11, 2026 94
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክርና ኢኮኖሚ ዕድገትን ለማፋጠን የሚያስችል የጋራ መግባባት ይገነባል የሚል ተስፋ አለን ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል መካሄዱን ቀጥሏል። በጉባኤውም በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ የሕዝብ ወኪሎች፣በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንዳሉት፣ የምክክር ጉባኤው በኢትዮጵያውያን መካከል የጋራ መግባባትን በመፍጠር ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ወሳኝ መንገድ እንደሆነ ከፍተኛ እምነት አላቸው። የምክክር ሂደቱ የሀገርን አንድነት ለማጠናከር፣ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማሳደግ የሚያስችል የጋራ መግባባት እንደሚፈጥር ትልቅ ተስፋ የጣሉበት መሆኑንም ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪ የመዲናዋ ነዋሪዎች መካከል ሮቤል ብርሃኑ፣ ሀገራዊ ምክክር በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን የሚገነባ አዋጭና ስልጡን አካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። በሀገራዊ ችግሮች ዙሪያ በአንድ ጣሪያ ሥር ምክክር ሲደረግ፣በመሠረታዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባትን ለመገንባት የሚያስችል ወሳኝ መንገድ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በፖለቲካው መስክ መግባባትን በመፍጠር የሀገርን የኢኮኖሚ አቅም የሚገነባ የተረጋጋ የልማት ሥራን ለማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤም የኢኮኖሚ ዕድገትና የሕዝብ አንድነትን የሚያጠናክር የጋራ መግባባት የሚገነባ አዎንታዊ ምክረ ሐሳቦች የሚፈልቁበት እንደሚሆን ተስፋ አለኝ ብለዋል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ኃይሌ ዓለማየሁ በበኩላቸው፣ የአንድ ሀገር ዜጎች በጋራ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የምክክር ሐሳብ በመወጠን መሰባሰባቸው በራሱ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል። ከዚህ ታሪካዊ መድረክ በኋላም የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያሳልጥ የጋራ መግባባትን በመገንባት፣ኢትዮጵያ በአፍሪካ ደረጃ መሪ ሀገር ለመሆን የሚያስችላትን አቅም እንደምትፈጥር እምነታቸውን ገልጸዋል። የምክክር ጉባኤው አካታችነት በዜጎች መካከል የጋራ መግባባትን በመገንባት የሕዝብ አንድነትን ይበልጥ ያጠናክራል የሚል ተስፋ አለኝ ያሉት ደግሞ ያደታ ጉደታ ናቸው። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ አልማዝ ታምራት በበኩላቸው፣ የምክክር ጉባኤው በዜጎች መካከል ጠንካራ መግባባት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት መሠረት የሚጥል የጋራ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። የመዲናዋ ነዋሪ አስቻለው በርጋ እንዲሁ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመፍጠር የሚያግዝ ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል። አቶ ገረመው ደበበ በበኩላቸው፣ የሀገራዊ ምክክሩ ውጤትም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘላቂ ሰላምና የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን የጋራ መግባባት ይፈጥራል የሚል እምነት አለኝ ብለዋል።
ኢትዮጵያን ማስቀደም፡ሀገራዊ ምክክሩና የዜጎች ዘላቂ መግባባት የመፍጠር ቁርጠኝነት
Aug 11, 2026 197
ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ በመመካከር ዘላቂ መግባባት ላይ ለመድረስ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያሳየው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በዜጎች የነቃ ተሳትፎ መካሄዱን ቀጥሏል። ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው ይህ ታሪካዊ ጉባኤ፣ በኢትዮጵያ ዘመናት የተሻገሩ ውስብስብ ችግሮችንና ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት የመፍታት አዲስ ባህል እየገነባ ይገኛል። ተመካካሪዎች በስምንት አጀንዳዎች በመካከር ላይ ይገኛሉ። አጀንዳዎቹ የተለዩት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ካደረገ በኋላ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የቀረቡት ስምንቱ አጀንዳዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ ድምፅ፣ ቅሬታ፣ ፍላጎት፣ ተስፋና ስጋት የተቀዱ መሆናቸውን ኮሚሽኑ አመልክቷል።   ኮሚሽኑ በማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 በተሰጠው ስልጣን መሰረት፣ የህዝብን ቀጥተኛ ተሳትፎ ያረጋገጠና "ከታች ወደ ላይ" የሚለውን ስልት የተከተለ አካታችና ሁሉን አቀፍ ስራ ማከናወኑን አስታውቀዋል። የሀገር ግንባታ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር እንዲሁም ሰላም ግንባታ ምክክር እየተደረገባቸው ያሉ አጀንዳዎች ናቸው። የሕዝቦችን አሰባሳቢ እሴቶች ለማጠናከርና የተራራቁ ትርክቶችን ወደ አንድነት ለማምጣት ያለመው ይህ የምክክር ሂደት፣በአሁኑ ወቅት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ከነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከስልታዊ ቡድኖች የቀረቡ የአጀንዳ ምክረ-ሃሳቦች ተቀናጅተው ለስራ ቡድኖች መቅረብ የጀመሩ ሲሆን፣ምክረ ሀሳቦቹን የማቅረብ ሂደት ዛሬም ቀጥሎ እየተካሄደ ይገኛል። በዚህም በተጠናቀሩት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ያተኮረ ሰፊ ውይይት ቀጥሎ በመካሄድ ላይ ነው። በእያንዳንዱ 500 አባላት ባሉት 8 የስራ ቡድኖች ውስጥ ከተመረጡ 30 ተወካዮች የቀረቡት እነዚህ ሃሳቦች፣ ወደ አካታችና የመጨረሻ ምክረ-ሃሳብነት እንዲያድጉ በጥልቀት እየመረመሩ ይገኛሉ። በጉባኤው ላይ 4000 በቀጥታ የሚሳተፉ ተመካካሪዎች የተገኙ ሲሆን፣ እነዚህም በስምንት ተመካካሪ ቡድኖች ተከፋፍለው በስምንት ቁልፍ የምክክር አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት በመወያየት ላይ ይገኛሉ። ሂደቱን በስልትና በስርዓት ለመምራት 16 ስልታዊ ቡድኖች፣160 አመካካሪዎች፣ 158 ቃለ-ጉባኤ ያዦች እንዲሁም የሙያ ድጋፍ የሚሰጡ 80 የባለሙያዎች ቡድን (Panel of Experts) ተመድበው በቅንጅት እየሰሩ ነው። በተጨማሪም የሁሉንም ወገን ድምፅ ለማካተት ሲባል 336 የክልልና የፌዴራል ተወካዮች በሂደቱ ላይ በነቃ ሁኔታ በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል። ይህ ምክክር ዜጎች ከግል፣ከቡድን ወይም ከአካባቢያዊ እሳቤዎች ሙሉ በሙሉ በመውጣት ኢትዮጵያን በማስቀደም እየተካሄደ ይገኛል። ሕብረተሰቡ በየደረጃው የሚያደርገው የነቃ፣ግልጽና አካታች ተሳትፎ፣በኢትዮጵያ የጋራ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ባህልን ከማሳደጉም በላይ የዜጎችን እውነተኛ ባለቤትነት ያረጋገጠ ነው። ይህ ሀገራዊ ምክክር ለሀገር ዘላቂ ሰላም፣ወንድማማችነትና የጋራ ዕድገት ጽኑ መሰረት የሚጥል ታሪካዊ ክስተት ነው። ዜጎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሙሉ ነፃነትና ተስፋ ተወያይተው የጋራ መግባባት በመፍጠር፣ ሀገራቸውን ወደ ተሻለ የልማትና የስልጣኔ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችላቸውን አዲስ ተስፋ በጋራ በመገንባት ላይ ይገኛሉ።
የምክክር ጉባኤው ሂደት ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው
Aug 10, 2026 789
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሂደት ወደ ማጠቃለያው ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ፡፡ የምክክሩ አካሄድ የውሳኔ የመስጠት ሂደት ሳይሆን ምክረ ሀሳብ ማቅረብ መሆኑንም አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ የምክክር ሂደቱን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ በሰጡት መግለጫ፣ የምክክር ሂደቱ እየተጠናከረና ወደ ተሻለ ደረጃ እየተሸጋገረ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ከዚህ ቀደም ከ10 እና ከ50 ተሳታፊዎች ተነስተው የነበሩ ሀሳቦች ወደ 250 ቡድኖች ማደጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡ አሁን ባለው ደረጃ ሁለቱ የ250 ቡድኖች የተነጋገሩባቸውንና የሰሯቸውን ስራዎች አጠናቅረውና ሰንደው ለ500ዎቹ ቡድኖች ማቅረብ መጀመራቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የቀጣዩን ምዕራፍ የጀመሩ የ500 ቡድን አባላት የቀረቡላቸውን ሀሳቦች በማዳመጥ፣መካተት ያለባቸውንና የሚገባቸውን ሀሳቦች በደንብ እያዳበሩ ይገኛሉ ብለዋል። እስካሁን 250 ሆነው በመወያየት ላይ የሚገኙ ተመካካሪዎች ዛሬ ከሰዓት በኋላ የሚጨርሱ እና ነገ ጠዋትም የሚጨርሱት ደግሞ ነገ ከሰአት በኋላ ለ500 ቡድኖቻቸው የሚያቀርቡ ይሆናል ብለዋል። በሂደቱ መጀመሪያ ላይ የተለያዩ አስተያየቶች፣ ክርክሮች እና የተለያዩ ስሜት መንጸባረቆች መታየታቸው የምክክሩን አሳታፊነት እና ህያውነት የሚያሳዩ ተፈጥሮአዊ የውይይት ማሳያዎች መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ የተለያዩ ሀሳብ የመስጠት ፍላጎቱ የሚመጣው ተሳታፊዎች የየራሳቸውንና የረጅም ጊዜ ጥያቄዎቻቸውን ለማንጸባረቅ ትክክለኛው አጋጣሚ ነው ብለው ስለሚያምኑ ነው ብለዋል። አልፎ አልፎ የሚታዩ ስሜታዊነት በምክክር ኮሚሽኑ የስብሰባ ስነ-ስርዓት ደንብ በጭራሽ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። በምክክር ሂደቱ ውስጥ አንደኛው መርህ መከባበር ሲሆን፣ ሁለተኛው መነጋገር፣ መደማመጥና ወደ መሀል መምጣት በመሆኑን ተመካካሪዎች ይህንን ሊያጠናክሩ ይገባል ብለዋል። ተሳታፊዎች የመጡት በየመንደሩና በየአካባቢው ያለውን ጥያቄ እዚያው እንዲመለስ ለማድረግ ሳይሆን ኢትዮጵያን ማዕከል አድርገው መመካከር እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡ የምክክሩ አካሄድ የውሳኔ የመስጠት ሂደት ሳይሆን ምክር ሀሳብ ማቅረብ መሆኑን ጠቁመው፤ ምክረ ሀሳቦቹ ለህግ አስፈጻሚው፣ ለህግ አስከባሪው፣ ለህግ አውጪው፣ ለህግ ተርጓሚው፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎችና ለሲቪል ማህበራት የሚተላለፉ ናቸው ብለዋል። "በድምፅ ብልጫ ውሳኔ ይሰጣል" ወይም "ከውስጥና ከውጭ ጫና ተደርጎ ውሳኔ ሊያስተላልፉ ነው" የሚባለው ወሬ ከአሉባልታ ያለፈ አይደለም ብለዋል። በአሁኑ ሰዓት በተመካካሪዎች መካካል የሚታዩ ክርክሮችና አለመግባባት በ"ዳይቨርጀንስ" (የመበታተን) ምዕራፍ ላይ ያለ በመሆኑ አግባብነት ያለውና ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል። ወደ መሰብሰብ ምዕራፍ (ኮንቨርጀንስ) ስንመጣ የራሳችንን የግል ሀሳብ እየጣልን ኢትዮጵያን ማዕከል ያደረገ የጋራ ሀሳብ ይዘን እንሄዳለን ብለዋል። በጣም ያጨቃጭቃሉ ተብለው የነበሩ አጀንዳዎች ቀደም ብለው ህዝቡ "የጋራችን ነው" በማለት ወደ መሀል ያመጣቸው ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል። ምክክሩ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው ከአንድ ወር ልፋት በኋላ በሚቀጥሉት አንድ እና ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከ4ሺህ ተሳታፊዎች ጋር ያለው የምክክር ሂደት ይገባደዳል ብለዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ኮሚሽኑ የመጡት ሀሳቦች አጠናክሮ ለተግባራዊው አካል የሚላኩ ሲሆን፣ መተግበራቸውም እየተከታተለ ለህዝብ ይፋ ይደረጋል ብለዋል። ዋና ኮሚሽነሩ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ሆነው ሂደቱን በትህትና ለሚከታተሉ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
​​​​​​​በምክክር ጉባኤው የሚተላለፍ ውሳኔ የለም - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ
Aug 10, 2026 738
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የሚተላለፍ ውሳኔ እንደሌለና ዋና ዓላማው ለተግባራዊ አካላት ምክረ ሀሳቦችን ማዘጋጀት መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። ከ10ሩ ቡድኖች የተውጣጡ ሁለቱ የ250 አባላት ስብስብ ያዘጋጁትን ሃሳብ በጋራ እያጠናቀሩ እንደሚገኝ ዋና ኮሚሽነሩ አመልክተዋል። በመቀጠልም እነዚህ ሁለቱ የ250 ቡድኖች በጋራ በመሆን ለ500 አባላት የተወያዩባቸውን ሀሳቦች ለ500ዎቹ እያቀረቡ እንደሚገኝና ይህ ሂደት ቀጣይነት እንዳለው ጠቁመዋል። ባለ 500ዎቹ የአጀንዳ ቡድኖች በሃሳቦቹ ላይ አስተያያት በመስጠት አጀንዳዎቹ እንዲዳብሩ እያደረጉ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በአሁኑ ሰዓት የ500 ምክክር መጀመሩንና ሁሉም የ500 ተመካካሪ ቡድኖች በሁለት ቀናት ሙሉ ለሙሉ ወደ ምክክር እንደሚገቡም ጠቁመዋል። ከተለያዩ ማህበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ተመካካሪዎች የተለያዩ ሀሳቦችና ጥያቄዎችን በማንሳት እየመከሩ እንደሚገኝና አጠቃላይ ሂደቱ ጥሩ የሚባል እንደሆነ አንስተዋል። በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የሚወሰን ውሳኔ የለም ያሉት ዋና ኮሚሽኑ የሂደቱ ዋና አላማ ምክረ ሀሳቦችን ማቅረብ ነው ብለዋል። በጉባኤው የሚቀርቡ ምክር ሀሳቦች መንግስት እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ጨምሮ በተግባሪ አካላት እንደሚፈጸሙ አስገንዝበዋል። በምክክሩ ላይ እንደዚህ አይነት ውሳኔዎች ሊተላለፉ ነው የሚሉ ሀሳቦች ከአሉባልታ የዘለለ ትርጉም እንደሌላቸው ተናግረዋል። የምክክር ጉባኤው አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ የተለያዩ የማይስማሙ ሀሳቦች መነሳታቸው አግባብና ተፈጥሯዊ ሂደት መሆኑን ጠቅሰው ይህም በቀጣይ ሀሳብን ወደ መሐል ለማምጣት ሂደት ወሳኝ መሰረት እንደሚጥል ነው ያነሱት። የመሰባሰብ ምዕራፍ ላይ ሲደርስ የግል ሀሳቦች እየተጣሉ ኢትዮጵያን ያማካሉ የጋራ ሀሳቦች እንደሚመጡም አንስተዋል። በስምንቱ አጀንዳዎች ላይ የሚደረጉ ውይይቶች በቀጣይ የተሻለ ምክረ ሀሳቦች እንደሚገኝባቸው ዋና ኮሚሽነሩ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ እየተካሄደ ይገኛል።
በሃገራዊ ምክክሩ ባለ 500 ተመካካሪ ቡድኖች የቀረቡላቸውን ሃሳቦች እያዳበሩ ይገኛሉ - መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)
Aug 10, 2026 682
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ባለ 500 ተመካካሪ ቡድኖች 250 አባላት ባሏቸው ስልታዊ ቡድኖች የቀረቡላቸውን ሃሳቦች እያዳበሩ እንደሚገኙ የሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ገለጹ፡፡ ዋና ኮሚሽነሩ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን አሁናዊ ሂደት አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ። ከነሃሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከስምንቱም ቡድኖች በተመረጡ 30 አባላት ከስልታዊ ቡድኖች የቀረቡ የአጀንዳ ምክረ ሃሳቦችን ተቀናጅተው 500 አባላት ላሏቸው 8 የስራ ቡድኖች መቅረብ መጀመራቸውን ጠቁመዋል። ይህ የምክክር ደረጃ 500 ተመካካሪዎች በሚወያዩበት አጀንዳ ላይ የመጨረሻ ምክረ ሀሳብ ለማቅረብ ጥልቅ ውይይት የሚያደርጉበት መሆኑንም ገልጸዋል። በእነዚህ የተጠናቀሩ የአጀንዳ ሃሳቦች ላይ የመወያየቱ ሂደት እስከ ዛሬ ድረስ የቀጠለ መሆኑን ገልጸው 500 አባላት ላሏቸው 8 የስራ ቡድኖች የቀረቡ ሃሳቦችን እያደበሩ ይገኛሉ ብለዋል። በስልታዊ ቡድኖቹ የቀረቡላቸውን አጀንዳዎች አዳብረው የጨረሱ እንዳሉ ሁሉ ያላጠናቀቁ ቡድኖችም በሚጨርሱበት ጊዜ ቀጣዩ ቡድን እንደሚያስረክቡ ተናግረዋል።
ማህበራዊ
በኦሮሚያ ክልል የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Aug 11, 2026 52
ጅማ ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የወጣቶች ክንፍ የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ረሂማ ዩሱፍ አስታወቁ። በጅማ ዞን በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በዞኑ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች የደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካሞች ቤት ዕድሳት እና ሌሎች የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች ተጠናክረው እየተከናወኑ ይገኛሉ።   በዛሬው ዕለትም በዞኑ ማና እና ጎማ ወረዳዎች ለአቅመ ደካማ ወገኖች በበጎ ፈቃድ የተለያዩ ድጋፎች ተደርገዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የወጣቶች ክንፍ የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ረሂማ ዩሱፍን ጨምሮ የጅማ ዞን አስተዳዳሪ ቲጃኒ ናስር እና ሌሎችም የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል። የተደረገው ድጋፍ የአቅመ ደካማ ወገኖችን ሕይወት በዘላቂነት ለመቀየር ያለመ መሆኑም ተገልጿል። ከተደረጉት ድጋፎች መካከል የትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ፣ የምግብ ግብዓት፣ የንብ ቀፎዎች እና ዘመናዊ የኤክትሪክ ምጣድ ይገኙበታል።   ወይዘሮ ረሂማ በወቅቱ፤ በክልሉ በርካቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቅሰው፤ በዚህ ውስጥ የወጣቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ነው ብለዋል። ሁሉም በያለበት በመተባበር በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚያደርገውን ተሳትፎ እንዲያጠናክርም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፤ በዘንድሮው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በዞኑ ከ5 ሺህ 500 በላይ የአቅመ ደካሞችን ቤት ለማደስ ታቅዶ እስካሁን ከግማሽ በላይ የሚሆኑት መታደሳቸውን ተናግረዋል።   የተደረገው ድጋፍ የዕለት ብቻ ሳይሆን ዘላቂነት ያለው መሆኑን የገለጹት አስተዳዳሪው፤ ድጋፉ የተደረገላቸው ወገኖች ሰርተው ሕይወታቸውን መለወጥ እንዳለባቸው አሳስበዋል። በማና ወረዳ በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር እስካሁን ከ300 በላይ የሚሆኑ የአቅመ ደካሞች ቤቶች መጠገናቸውን የገለጹት ደግሞ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሰመሩዲን አህመድ ናቸው።   ከዚህ በተጨማሪ የደም ልገሳ እና ሌሎችም ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እገዛ ብቻ ሳይሆን እንደ ገዳ ስርዓት ነባር የመተሳሰብ እና የመደጋገፍ ባህላችን ነው ብለዋል።   ድጋፍ ከተደረገላቸው መካከል የማና ወረዳ ነዋሪዎቹ ወይዘሮ ፋጡማ አባገሮ እና ትዕግስት ጌታቸው፤ የተደረገላቸው ድጋፍ የዕለት ጉርስ ብቻ ሳይሆን በዘላቂነት ህይወታቸውን የሚቀይር መሆኑ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል። በቀጣይ ሰርተው በመለወጥ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሌሎችን እንደሚደግፉ ቃል ገብተዋል።
ስልጠናው ከሳይንሳዊ እውቀት በተጨማሪ የስራ ተነሳሽነታችን የፈጠረ ነው -መምህራን
Aug 11, 2026 52
ባህር ዳር፤ ነሃሴ 5/2018(ኢዜአ)፡- የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናው ሳይንሳዊ እውቀትና ክህሎትን ከማሳደግ ባሻገር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ተነሳሽነትን ፈጥሮልናል ሲሉ በባህር ዳር ከተማ ስልጠና በመውሰድ ላይ ያሉ መምህራን ተናገሩ። በባህር ዳር ከተማ እየተሰጠ ያለውን ስልጠና የሚከታተሉ መምህራን እንደገለጹት፤የክረምት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናው እውቀትና ክህሎታቸውን በማሳደግ ከፍተኛ አቅም ፈጥሮላቸዋል። ከሰልጣኞቹ መካከል መምህር ሀብታሙ ወንድሜነህ፣ስልጠናው በአብዛኛው ተግባር ተኮር በመሆኑ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። በተለይ "ተማሪዎችን በአካባቢያቸው ከሚገኙ ተጨባጭና በሚዳሰሱ ቁሳቁሶች ላይ ተመስርቶ በማስተማር የፈጠራ ችሎታቸውን ማዳበር እንደሚገባ እውቀት አግኝቻለሁ" ብለዋል። የእንግሊዘኛ ቋንቋ መምህር የሆኑት ነጻነት አለምነህ በበኩላቸው ፤ ስልጠናው ለተማሪዎች አራቱን መሰረታዊ የቋንቋ ክህሎቶች በቀላሉ ለማስተላለፍ የሚያስችል ዘዴና እውቀት እንዳስጨበጣቸው ተናግረዋል። የነበሩ ክፍተቶችን በመለየትና የትምህርት እቅድ አወጣጥን የተሻለ በማድረግ የመማር-ማስተማር ሂደቱን የተቃና ለማድረግ እንደረዳቸውም ነው የጠቆሙት። የመምህራን አቅም መጎልበት ለትውልድ ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ስልጠናውን በከፍተኛ ፍላጎት እየተከታተሉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። የአጠቃላይ ሳይንስ መምህርቷ ወርቃለም መኮንን ፤በስልጠናው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አዳዲስ የማስተማር ዘዴዎችን መቅሰማቸውን ጠቁመዋል። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ትበይን ባንቲሁን፤ የትምህርት ጥራት መሰረት ለሆኑት መምህራን የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በክረምቱ የተመደበውን ኮታ ሙሉ በሙሉ በመጠቀም መምህራን፣ ርዕሳነ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች እንዲሰለጥኑ መደረጉን ተናግረዋል። ስልጠናው በዩኒቨርሲቲ መምህራን የሚሰጥ በመሆኑ መምህራን በተነቃቃ መንፈስ ተማሪዎቻቸውን እንዲቀበሉና የተሻለ የመማር-ማስተማር ስርአት እንዲዘረጉ ያለመ መሆኑንም አብራርተዋል። በአማራ ክልል በክረምቱ ወቅት ከ10 ሺህ በላይ መምህራንና የትምህርት አመራሮች በ11 የስልጠና ማዕከላት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
ሪፈራል ሆስፒታሉ በሚሰጠው ነፃ የምርመራና የህክምና አገልግሎት በርካቶችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው
Aug 11, 2026 145
ሮቤ፤ ነሐሴ 5/2018(ኢዜአ)፡- በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በርካቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ ነፃ የምርመራና ህክምና አገልግሎቶች በመስጠት ላይ ይገኛል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጎባ ሪፈራል ሆስፒታል በክረምት ወራት በሚያካሄደው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አማካኝነት ለአካባቢው ህብረተሰብ ነፃ የምርመራ፣ የህክምና እና የቀዶ ጥገና አገልግሎቶችን ሲሰጥ ቆይቷል።   በዚህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎት ሀላፊነቱን ከመወጣት ባለፈ፣ የህክምና ወጪን መሸፈን ለማይችሉ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ወገኖች ትልቅ እፎይታን ፈጥሯል። የሪፈራል ሆስፒታሉ ዋና ስራ አስፈጻሚ ተባባሪ ፕሮፌሰር መሐመድአማን ማማ ለኢዜአ እንዳሉት ሪፈራል ሆስፒታሉ የተሻለ የህክምና አገልግሎት ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እያደረገ ነው። በተለይም በመደበኛነት ከሚሰጠው የህክምና አገልግሎት ባሻገር በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በተለያዩ ችግሮች ወደ ህክምና ተቋማት መሄድ ያልቻሉ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።   አገልግሎቱ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር እና ራሳቸውን ሳያውቁ ለተለያዩ በሽታዎች የተጋለጡ ሰዎች ተገቢውን ህክምና እንዲከታተሉ የማስቻል ዓላማ ማድረጉንም አክለዋል። በዚህም በክረምቱ ወቅት ከ120 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች አገልግሎት ለመስጠት አቅዶ እስከ አሁን 150 ሺህ የሚሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንና ሥራውም ተጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚው እንዳሉት በዘንድሮ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት እየተሰጡ ከሚገኙት ነፃ የምርመራና የበሽታ ልየታ አገልግሎቶች በተጓዳኝ በመደበኛው የህክምና አገልግሎት ወቅት የቀዶ ህክምና ወረፋ ሲጠባበቁ የነበሩ ህሙማን ጭምር የሚስተናገዱበት አሰራር መመቻቸቱ መርሃግብሩን ልዩ ያደርገዋል። በዩኒቨርሲቲው የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጤና ትምህርትና ህክምና አገልግሎት ኮርፖሬት ዳይሬክተር አቶ አቤል በልሁ በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው ለማህበረሰቡ ከሚሰጠው የምርመራና የህክምና አገልግሎት በተጓዳኝ በበሽታ ተጋላጭነትና መተላለፊያ መንገዶቹ ላይ ተከታታይነት ያለው ግንዛቤ እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።   "በጎነት ለጤናችን'' በሚል መርህ እንደ ሀገር በተጀመረው የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ከጤና ባሻገር የችግኝ ተከላ፣ የደም ልገሳ እና ሌሎች በጎ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አውስተዋል። በሆስፒታሉ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ዘመቻው አስተባባሪ ጠቅላላ ሐኪም ዶክተር ሰለሞን ክፍሌ በበኩላቸው እንዳሉት፤ የህክምና ባለሙያዎቹ ቡድን ከሚሰጡት አገልግሎት መካከል የደም ግፊት፣ ኤች.አይ.ቪ፣ የስኳር በሽታ፣ የጡት ካንሰር፣ የጉበት በሽታ፣ የዓይን ምርመራና የሌሎች በሽታዎች ልየታና ህክምና ይገኙበታል።   የሕክምና ቡድኑ በሚኖረው ቆይታ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎችን የመለየትና የምርመራና የህክምና አገልግሎት ከመስጠት በተጓዳኝ ተጨማሪ ህክምና የሚያስፈልጋቸውን ህሙማን በመለየት ለተጨማሪ ምርመራና ህክምና ከሆስፒታሉ ጋር የማገናኘት ስራ እንደሚሰሩም አስረድተዋል፡፡ ከነፃ ህክምናው ተጠቃሚዎች መካከል ወይዘሮ አልፊያ ሁሴን እንዳሉት ሆስፒታሉ በጀመረው ዘመቻ በቀላሉ ህክምና በማግኘት ያሉበት የጤና ደረጃ ለማወቅ አስችሏቸዋል። አቶ አህመድ መሐመድ በበኩላቸው የህክምና ባለሙያዎች በነፃ በሰጡት የምርመራ አገልግሎት ከበሽታ ስጋት ነፃ በመሆናቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል። በአገልግሎቱ ሰዎች በበሽታ ከመጎዳታቸው በፊት ራሳቸውን አስቀድመው እንዲያውቁ ያገዛቸው በመሆኑም ተቋሙን አመስግናዋል።
በአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የተጀመሩ ውጤታማ የለውጥ ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Aug 11, 2026 81
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የተጀመሩ ውጤታማ የለውጥ ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ዓለምአንተ አግደው ገለፁ። የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ክንውን እና የ2019 የትኩረት አቅጣጫዎች የውይይት መድረክ በባህር ዳር ከተማ ተጀምሯል። ፕሬዝዳንቱ አቶ ዓለምአንተ አግደው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ የፍርድ ቤቶችን አሰራር በቴክኖሎጂ ታግዞ በማዘመን በኩል ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።   በተለይ ቀደም ሲል ማህበረሰቡ በአሰራር ዙሪያ ያነሳቸው የነበሩ ቅሬታዎችንና አቤቱታዎችን በዘላቂነት ለመፍታት ባለፋት ሦስት ዓመታት የፍርድ ቤቶች የትራንስፎርሜሽን እቅድ ተግባራዊ መደረጉን አስታውሰዋል። በተቀናጀ አግባብ በተሰሩ የለውጥ የአሰራር ማሻሻያዎች፣ የዲጅታላይዜሽን ትግበራዎች እና የተቋማት ግንባታዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልፀዋል። በዚህም በፍርድ ቤቶች በሚታዩ መዝገቦች ቁጥር፣ የዳኝነት አሰጣጥ ጥራትና ፍጥነት ከፍተኛ መሻሻል መታየቱን አረጋግጠዋል። መደበኛ ፍርድ ቤቶች ግልፅና ተጠያቂነት ባለው መንገድ መዳኘት ያስቻለ የቴክኖሎጂ አሰራር ተግባራዊ በማድረግ ማዘመን እንደተቻለም ተናግረዋል። እንዲሁም አማራጭ የዳኝነት መስጫ ማዕከላትን ተደራሽ በማድረግም ዜጎች በአቅራቢያቸው ሆነው ያለምንም ወጭና ድካም የዳኝነት አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም አሰገንዝበዋል። ፍርድ ቤቶች ገለልተኝነትና ነፃነታቸውን በጠበቀ መንገድ ከተቋማት ጋር በጠንካራ ትብብርና ቅንጅት እየሰሩ እንደሆነም አስገንዝበዋል። የዳኝነትና የፍትህ አሰጣጡን በማዘመንና ተደራሽነታቸውን በማሳደግ ማህበረሰቡ የበለጠ የሚተማመንባቸው በማድረግ በኩል የተጀመሩ የለውጥና የዲጂታላይዜሽን ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል። በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ዙሪያ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል፤ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡም እውቅናም እንደሚሰጥ ነው የተገለፀው። የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን የለውጥ ስራ እና የዲጅታላይዜሽን ትግበራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባለፈው ሳምንት መጎብኘታቸው ይታወሳል።  
ኢኮኖሚ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል
Aug 11, 2026 26
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ አስታወቀ።   የቢሮው ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ለኢዜአ እንደገለጹት በግብርና፣ በአገልግሎት፣ በእንጨትና ብረታብረት እንዲሁም በሌሎች መስኮች የሥራ ዕድል በመፍጠር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተጀመሩ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል።   ቢሮው በ2018 በጀት ዓመት በግብርና፣ በአገልግሎትና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ለ400 ሺህ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ለመፍጠር አቅዶ ከ379 ሺህ 430 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ለመፍጠር መቻሉን ተናግረዋል። የሥራ ዕድል ፈጠራውን ውጤታማ ለማድረግም በበጀት ዓመቱ ከ925 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ብደር መመቻቸቱን፣ 8 ሺህ 420 ሄክታር መሬት መቅረቡን እና 689 አዳዲስና ነባር ሼዶች ለኢንተርፕራይዞች እንዲተላለፉ መደረጉን ተናግረዋል።   በበጀት ዓመቱ የሥራ እድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል በጉራጌ ዞን እምድብር ከተማ ነዋሪ ወጣት ዳዊት ትዛዙ እንዳለው ከመንግስት ባገኘው የገንዘብ ብድር በቅመማ ቅመም፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ መሰማራቱን ጠቁሟል። በአራት ሄክታር መሬት ላይ እያለማ ያለውን ቲማቲም ሽንኩርትና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን መጀመሩንም ተናግሯል።   በአሁኑ ወቅትም ከራሱ ባለፈ ለሌሎች ሥራ አጥ ወገኖች ጊዜያዊ ሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ገልጿል። በመንግስት ካገኘው የገንዘብ ብድር በተጨማሪ በተሰማራበት የእርሻ ሥራ ውጤታማ እንዲሆን በግብርና ባለሙያዎች ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግለትም ተናግሯል። ሌላው በሆሳዕና ከተማ ነዋሪ ወጣት ዳንኤል አሰፋ በበኩሉ በከተማው በሚገኘው ታዴ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ኢንተርፕራይዝ ቋሚ የሥራ ዕድል እንደተፈጠረለት ገልጿል።   በዚህም በሚያገኘው ገቢ እራሱን ከማስተዳደሩ በተጨማሪ ነገ የራሱን ሥራ በመፍጠር ሕይወቱን የተሻለ ደረጃ ላይ ለማድረስ ራዕይ እንዲሰንቅ ማድረጉን ተናግሯል።  
በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል
Aug 11, 2026 79
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ ህገወጥነትን በመከላከልና በማጋለጥ በኩል ህብረተሰቡ ተሳትፎውን ማጠናከር እንዳለበትም ጠቁመዋል። መንግሥት በተደራጀ ሙስናና ሕገወጥ ድርጊቶች የተሰማሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል የሕግ የበላይነትን እያረጋገጠ እንደሚገኝ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በሰጠው መግለጫ አሳውቋል፡፡ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት ከልማት ሥራዎች ባሻገር የሕግ የበላይነትን ማስፈን ቀዳሚ ተግባሩ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ የመንግሥትን ሕግ የማስከበር ርምጃ በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ የህዝብን ሀብት ከምዝብራና ብክነት መጠበቅ የመንግሥት ትኩረት ሊሆን ይገባል፡፡ በቅርቡ መንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊቶች ላይ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ስር በማዋል ተጠያቂነትን ለማስፈን የወሰደው እርምጃ ተገቢና ቀጣይነት ሊኖረው የሚገባ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከአስተያየት ሰጭዎች መካከል ሄኖክ ተስፋዬ፤ ርምጃዎቹ የሕግ የበላይነትን በማስፈን የመንግስትና የህዝብን ሀብት ከምዝበራ ማዳን ነው ብለዋል፡፡ በብልሹ አሰራርና ባልተገቡ አሰራሮች ላይ እየተወሰደ ያለው ርምጃ የመንግሥትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እና በዜጎች ዘንድ ደግሞ መተማመንን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡   ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ትዕግስት ገብረየስ፤ መንግሥት ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚወስደው ርምጃ እስከታች ባለው የመንግሥት መዋቅር ገቢራዊ መደረግ አለበት ብለዋል፡፡ መንግሥት ተጠያቂነትን ለማስፈን የጀመረው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በማንሳት፤ ሂደቱ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ወጣት ቴዲ ዑለማ በበኩሉ፤ መንግሥት የህግ የበላይነትን ለማስፈን የተግባር ቁርጠኛ መሆኑን ያሳየ ርምጃ መሆኑን ተናግሯል፡፡   ሌላው አስተያየት ሰጪ አቢቲ ረጋሳ ሙስናና ብልሹ አሰራር የዕድገት ማነቆ መሆኑን በመግለጽ፤ ርምጃው አስተማሪና ትምህርት ሰጭ ነው ብለዋል፡፡   ማንም ሳይለፋና ሳይሰራ መበልጸግ የለበትም፤ ሙሰኞችን ለህግ ማቅረብ ተጠናክሮ መቀጠል ህዝቡም መተባበር አለበት ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በለጡ ዘላለም ናቸው፡፡      
በጉጂ ዞን ለመኸር አዝመራ ከተዘጋጀው መሬት ከ106 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል
Aug 11, 2026 70
አዶላ፣ ነሐሴ 5/2018(ኢዜአ) ፡-በጉጂ ዞን ለመኸር አዝመራ ከተዘጋጀው መሬት እስካሁን ከ106 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው በተለያዩ የሰብል ምርጥ ዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡ በኦሮሚያ ክልል የጉጂ ዞን በቆላማ፣ በደጋ እና በወይና ደጋ አየር ንብረቶች የተከፋፈለ በመሆኑ የተለያዩ የሰብል ዓይነቶችን ለማምረት አመቺ ተፈጥሮ አለው። በዞኑ ከነሐሴ እስከ መስከረም አጋማሽ የዝናብና የዘር፣ እንዲሁም ከታኅሣሥ እስከ ጥር መጨረሻ የምርት ስብሰባ ወቅት ሲሆን፤ በመኽር ወቅት በብዛት ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል በቆሎ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍ፣ ቦሎቄ እና ዘይት ነክ ሰብሎች ይጠቀሳሉ።   በዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ መንግሥቱ ሂርባዬ እንደገለጹት፤ ለተያዘው የመኸር አዝመራ 498 ሺሕ 778 ሄክታር መሬት በተለያዩ ምርጥ የሰብል ዘር በማልማት ከ13 ሚሊዮን 200 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል። በተያዘው የመኽር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉ የግብርና አሠራሮችን መተግበርና ግብዓቶችን በአግባቡ መጠቀም ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል። በዚህም መሠረት የሜካናይዜሽን እርሻን ማስፋፋት፣ በኩታገጠም የመሬት ዝግጅትና በመስመር የመዝራት ዘዴዎችን በመጠቀም ረገድ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በመኽር ልማቱ እስከ አሁን በተደረገው እንቅስቃሴ፤ 119 ሺሕ 216 አርሶ አደሮችን በማሳተፍ 106 ሺሕ 159 ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም አሰራር በተለያዩ ምርጥ የሰብል ዘሮች መሸፈኑን አስታውቀዋል። በዞኑ በመኽር አዝመራው ከሚለሙት የተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መካከል፤ በዋናነት እንደ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ እና ቦለቄ ያሉ የእህልና የጥራጥሬ ሰብሎች ይጠቀሳሉ ብለዋል። ከግብዓት አቅርቦት አንጻርም በዞኑ ለሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች 12 ሺሕ 429 ኩንታል ምርጥ ዘር እና 71 ሺሕ 600 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ማቅረብ መቻሉን አስታውቀዋል። በእርሻው ተሳታፊ ከሆኑት አርሶ አደሮች መካከል በዞኑ የአዶላ ሬዴ ወረዳ የደራርቱ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ኔንቆ ዋሬ፤ ባለፈው የምርት ዘመን የተሻሻሉ የግብርና አሠራሮችን በመተግበር ካለሙት የእርሻ መሬት የተሻለ ምርት መሰብሰባቸውን ያስታውሳሉ። ካለፈው ዓመት ያገኙትን በጎ ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፤ በዘንድሮው የመኽር እርሻ በኩታ ገጠም ለማልማት ካዘጋጁት ማሳ ከፍተኛ ምርት ለማግኘት አልመው በትጋት እየሠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል።   የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ ማቴዎስ አዱላ በበኩላቸው፤ ለምርት ዘመኑ የሚያስፈልጉ የግብርና ግብዓቶች በወቅቱና በበቂ ሁኔታ እንደቀረበላቸው አንስተው፣ የታቀደውን ምርትና ምርታማነት ለማሳካት የግብርና ባለሙያዎች በቅርበት ዕገዛ እያደረጉላቸው መሆኑን አክለዋል። የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ የሰብል ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ የጠቆሙት አርሶ አደሩ፤ አሠራሩ አላስፈላጊ ወጪንና ጉልበትንም የሚቀንስ ነው ብለዋል።  
የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የቱሪዝም ዘርፉን የሚያነቃቃና ለከተማዋም ተጨማሪ ድምቀት ነው
Aug 11, 2026 149
አርባ ምንጭ፤ ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በገበታ ለትውልድ መርሐግብር የተገነባው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የቱሪዝም ዘርፉን የሚያነቃቃና ለከተማዋም ተጨማሪ ድምቀት መሆኑ ተገለጸ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢኒሼቲቭ የተገነባውና የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነው አርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት በቅርቡ መመረቁ ይታወቃል። ኢዜአ ያነጋጋራቸው የአርባ ምንጭ ከተማ ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ አቶ ደስታ ደምበላ እንደገለጹት ሪዞርቱ ለአካባቢው ብሎም ለሀገር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ግዙፍ የልማት ፕሮጀክት ነው።   ሪዞርቱ የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል መሆኑንም ጠቅሰው፣ የቱሪዝምና የአገልግሎት ዘርፉን ከማነቃቃት ባለፈ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር አስተዋጾ እንደሚኖረው ተናግረዋል። ሪዞርቱ የተገነባበት ቦታ ለቱሪዝም ምቹ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ደስታ፣ በተለይ በዓባያ ሐይቅ ላይ የተገነባው ተንሳፋፊ ሬስቶራንት የተለየ በመሆኑ የጎብኚዎችን ቀልብ ይስባል ብለዋል ። እንደሃላፊው ገለጻ የአካባቢውን የቱሪዝም ፀጋዎች ይበልጥ እንዲታወቁ በማድረግ በኩልም ፋይዳው የጎላ ሲሆን ሀገራዊ ጠቀሜታም ከፍተኛ ነው ብለዋል። የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪው አፈወርቅ አለማየሁ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ያስገነቧቸው ፕሮጀክቶች የሀገርን ገጽታ በመሰረታዊነት የቀየሩ ናቸው።   ሪዞርቱ በአርባ ምንጭና አካባቢው የሚገኘውን የሸማ ጥበብ፣ የባህል፣ የምግብና የአልባሳት ሥራዎችን ለማስተዋወቅና ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ምቹ ዕድል ይፈጥራል ሲሉም አክለዋል። በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን አስታውሰው፣ በቀጣይም ለዜጎች በቋሚና በጊዜያዊነት ተጨማሪ የሥራ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ሙና ዮሐንስ ሪዞርቱ የከተማዋን ውበት አጉልቶ የሚያወጣ ተጨማሪ ፀጋ ነው ሲሉ ገልጸዋል።   ወጣት ታምራት በርገኔ በበኩሉ ሪዞርቱ የአርባ ምንጭ ከተማን ገጽታ ይበልጥ ከማድመቅ ባለፈ ቱሪስትን በመሳብ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልፆ፣ ይህም ለከተማዋና ለሀገር እድገት የሚኖረው አበርክቶ የጎላ ነው ብሏል።   አስተያየት ሰጪዎቹ በአርባ ምንጭና አካባቢው ሰፊ የቱሪዝም አቅም በመኖሩ ሪዞርቱ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ወደ ከተማዋ ለሚመጡ ቱሪስቶችና እንግዶች ምቹ ማረፊያ እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የቱሪዝም መዳረሻዎችን ከማስፋፋት ባለፈ የሀገር የኢኮኖሚ አቅምን ከፍ ለማድረግ ሚናው የጎላ ነው። ሪዞርቱ ከ1ሺህ 300 በላይ ሰዎችን የሚያስተናግድ የስብሰባ አዳራሽና በሐይቅ ላይ የተገነባ ልዩ ተንሳፋፊ ሬስቶራንትን ያካተተ እንደሆነም በወቅቱ ተመላክቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም "ሪዞርቱ የኮንፈረንስ ቱሪዝምን በማስፋፋት ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ መድረኮች ማዕከል የማድረግ ራዕያችንን ያጠናክራል፤ ለአካባቢውም ማህበረሰብ ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል" ሲሉ በወቅቱ መግለጻቸው የሚታወስ ነው።    
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ምህዳር ለመገንባት ወሳኝ የሆነውን ብቁ የሰው ሃይል የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል
Aug 11, 2026 49
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ምህዳር ለመገንባት ወሳኝ የሆነውን ብቁ የሰው ሃይል የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሂሚድ ገለጹ። 5ተኛው ዙር ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ የታዳጊዎች የስልጠና መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀምሯል።   መርሃ ግብሩ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሚያዘጋጀው ሲሆን በሳይበር ደህንነትና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ዝንባሌ ያላቸውን ታዳጊዎችና ወጣቶች ለማፍራት ያለመ ነው። የሳይበር ደህንነት፣ሶፍትዌር ልማት፣ኮዲንግ፣ አቪዬሽን፣የኤሮስፔስ ቴክኖሎጂ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች በመርሃ ግብሩ ተካተዋል። የሀርድ ዌር እና ሴኪዩሪቲ ዲዛይኖችን ማዘጋጀት የስልጠና መርሀ ግብር ሌላው የትኩረት ማዕከል ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤የኢትዮጵያን ዲጂታል ሽግግር ውጤታማ ለማድረግ የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው። ለዚህ ደግሞ በቁ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤አስተዳደሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሰው ሃይል የማፍራቱን ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል። የሰመር ካምፕ የስልጠና መርሃ ግብር የዚሁ አካል መሆኑን ጠቁመው፤ መርሃ ግብሩ የነገ የኢትዮጵያ ተስፋ የሆኑ ተተኪ ትውልድ በማፍራት ረገድ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። የስልጠና መርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ መጀመሩን አስታውሰው ፤ በአሁኑ ወቅት ስልጠናው በባህር ዳር፣ጅማ ፣ወላይታ ሶዶ፣ሀረማያ ዩንቨርስቲዎችን ጨምሮ በአስተዳደሩ ግቢ ውስጥ እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል።   የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ የቴክኖሎጂ አቅሙ የተገነባ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የጀመረው ተተኪ ትውልድ የማፍራት ስራ የሚያስመሰግን ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለመርሃ ግብሩ ስኬት ዩንቨርሲቲው የሚጠበቅበትን ድርሻ እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ሰልጣኞችም ኢትዮጵያን የማገልገል አደራ አለባቸሁ፤ለዚህ ደግሞ ስልጠናውን በአግባቡ ተከታትላችሁ ተገቢውን ክህሎት ልትጨብጡ ይገባል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል የመሶብ አገልግሎት የአፍሪካ ሀገራት በተሞክሮነት የሚጋሩት የመንግሥት አገልግሎቶች ማሳለጫ መሳሪያ ነው
Aug 10, 2026 607
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ዲጂታል የመሶብ አገልግሎት የአፍሪካ ሀገራት በተሞክሮነት የሚጋሩት የመንግሥት አገልግሎቶች ማሳለጫ መሳሪያ መሆኑን የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ ገለጹ:: ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ በኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎት የሚሰጡ የአንድ ማዕከል፣ የተንቀሳቃሽና የተቀናጀ መሶብ ዲጂታል አገልግሎቶችን ጎብኝተዋል።   የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ ዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚያገኙበትን ዕድል ፈጥሯል። ይህም ብልሹ አሠራርንና የመልካም አስተዳደር ውስንነቶችን በመቅረፍ፣ በመንግሥትና በዜጎች መካከል በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ያለው መተማመን እንዲጎለብት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የተበታተኑ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ማዕከልና በተቀናጀ አግባብ የሚመሩበትን ወሳኝ ዕድል በመፍጠር፣ የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ የተጀመረው የኢፌዴሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን ላይ በተንቀሳቃሽና በተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነቱ በእጅጉ መስፋፋቱን አስረድተዋል። የመሶብ አገልግሎትም የመንግሥት አገልግሎት ሥነ-ምኅዳር ውጤታማነትን በማሻሻል፣ እመርታዊ ውጤት እንዲመጣ እያደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል። የመሶብ ዋነኛ ዓላማ የዜጎችን የአገልግሎት እርካታ ማሳደግ መሆኑን በመጠቆም፣ ከመሶብ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ከ98 በመቶ በላይ የዜጎች የአገልግሎት እርካታ በማስመዝገብ ከፍተኛ ውጤት ማምጣቱን ጠቁመዋል።   በቀጣይም በፌዴራል፣ በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች እየተስፋፋ የሚገኘውን የመሶብ አገልግሎት ተደራሽነት የበለጠ በማጠናከር፣ የዜጎችን አገልግሎት ለማሳለጥ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። በስምንት ተቋማት ከ40 በላይ አገልግሎቶች የተጀመረው የመሶብ አገልግሎት፣ በአሁኑ ወቅት በአንዱ ማዕከል ብቻ ከ27 በላይ ተቋማት የሚሰጡትን ከ288 በላይ አገልግሎቶች እያቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል። መሶብ ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ” ሽግግርን በማፋጠን፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ የአገልግሎት ሥርዓት አካል ሆኖ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ዲጂታል የመሶብ አገልግሎት ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በተሞክሮነት የሚቀስሙት የመንግሥት አገልግሎቶችን ማሳለጫ ተምሳሌታዊ አብነት መሆኑንም አስረድተዋል። ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የሀገራት አምባሳደሮችም፣ ኢትዮጵያ በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያስመዘገበችውን እመርታዊ ውጤት፣ ልምድና ተሞክሮ እንዲቀስሙ ያለመ መሆኑን አንስተዋል። ይህም ዲፕሎማሲያዊ ትስስርን ለማጠናከር፣ ልምድ ለመለዋወጥና የትብብር ዕድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን አስረድተዋል። የመሶብ ሥራ ገና በመጀመሪያ ምዕራፍ ያለ ሲሆን፣ በቀጣይ የአገልግሎቶችን ቁጥር ማሳደግ፣ ዲጂታላይዜሽንን ማፋጠን፣ የመሶብ አገልግሎትን በሁሉም ከተሞችና ወረዳዎች ማስፋፋት እና ልምዱን ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ማካፈል ቀጣይ ትኩረቶች ይሆናሉ።    
ወጣቶች ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር እኩል መራመድ አለባቸው- የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ቤተልሔም ደሴ
Aug 10, 2026 133
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ ወጣቶች ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር እኩል በመራመድ ራሳቸውን በክህሎት ብቁ እንዲያደርግ የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ቤተልሔም ደሴ ጥሪ አቀረበች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀረበውን የኢትዮጵያ ወጣቶች የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭን እንዲቀላቀሉ እና የክረምቱ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት የተሳታፊዎችን ቁጥር ወደ 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተደረገውን ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስተናጋጅነት በኢኒሼቲቩ ዙሪያ የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ተካሂዷል። ‎በመቀጠል በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ልምዳቸውንና እይታቸውን ያካፈሉ አራት ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። በ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ላይ ታሪኳን ያካፈለችው የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ቤተልሔም ደሴ፤ የቴክኖሎጂ ሕይወቷ ከአስራ ሰባት ዓመት በፊት ገና የአስር ዓመት ታዳጊ ባለችበት ወቅት እና የዲጂታል አማራጮች ጨርሶ በሌሉበት ሁኔታ ውስጥ እንደተጀመረ ገልጻለች። ያለፈውን ጊዜ ከአሁኑ ጋር በማነጻጸርም፣ ዛሬ ላይ ቴክኖሎጂ በስፋት ተደራሽ በመሆኑ የአሁኑ ዘመን ወጣቶች ህልማቸውን ለማሳካት የሚያስችል ምቹ መንገድ እንዳላቸው አመላክታለች። ይህ ትልቅ ዕድል ቢኖርም ስኬት ግን ፈጣን እርምጃን እንደሚጠይቅ ያስገነዘበችው ቤተልሔም፤ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመጠባበቅ ወጥተው አሁኑኑ የለውጥ መሪ እንዲሆኑ፣ እንዲሁም ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር እኩል ለመራመድ ራሳቸውን በክህሎት በንቃት እንዲያበቁ ጥሪዋን አስተላልፋለች። ‎ለተጨማሪ መረጃ እና ለመመዝገብ፦ ethiocoders.et ‎#PMOEthiopia #DigitalEthiopia2030 #5MillionEthiopianCoders
ወጣት አዝመራው ታደሰ በኢትዮ ኮደርስ ኢኒሼቲቭ የስኬት ምዕራፍ
Aug 10, 2026 114
ወጣት አዝመራው ታደሰ የ 5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ተመራቂ ወጣት ባለሙያ ነው። ወጣቱ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ዙሪያ ባዘጋጀው የልምድ ልውውጥ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት ተሞክሮውን አካፍሏል፡፡ ወጣት አዝመራው በመርሐ ግብሩ ላይ እንዳለው ፥ ይህንን ታላቅ ዕድል በዩኒቨርሲቲ ቆይታው የመጨረሻ ዓመታት ውስጥ በመቀላቀል አስደናቂ የስኬት ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ወጣቱ ኮድ ማድረግን መማር ከጀመረበት ጥረት ተነስቶ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ኮደሮችን የሚያገናኝ ድረ ገጽ ወደ ማበልጸግ መሸጋገር መቻሉንና ዛሬ ደግሞ ፉል ስታክ ድረ ገጽ አልሚ መሆኑን አስረድቷል። በሰርተፍኬት ብቻ አትወሰኑ የሚለው ወጣት አዝመራው የተማራችሁትን በተግባር በማዋል እና በመለማመድ እውነተኛ ዕድገት ማምጣት ትችላላችሁ ሲል ተናግሯል። ‎በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ሥዩም እንዳሉት ፥ የወጣቶች የቴክኒክና የዲጂታል ክህሎት ብቃት ወሳኝ ሀገራዊ ሀብት ነው፡፡ በዚህ ክረምት የኮደሮችን ቁጥር 7 ሚሊየን ለማድረስ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበውን ጥሪ ተግባራዊነት አረጋግጠዋል።  
ስፖርት
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር አባል ሆነች
Aug 10, 2026 604
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር (World Boxing) ባወጣው መረጃ መሰረት የማህበሩ ስራ አስፈፃሚ ቦርድ ኢትዮጵያን ጨምሮ የስድስት አገራትን የአባልነት ጥያቄ ማፅደቁን አሳውቋል። ይህንኑ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ እያሱ ወሰን ባስተላለፉት መልዕክት፣ ኢትዮጵያ ማህበሩን በመቀላቀሏ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። አክለውም፣ ይህ ለኢትዮጵያ የኩራት ጊዜ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ አንድ የአፍሪካ የቦክስ ቤተሰብ ለሁላችንም የደስታና የክብር ወቅት ነው ሲሉ ተናግረዋል። ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም በአፍሪካ ስፖርቱን የሚያጠናክር እያንዳንዱ እርምጃ ለሁሉም ድል መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህ ታሪካዊ ምዕራፍ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ሁሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ አዲሱ ምዕራፍ ለአፍሪካ ቦክስ ታላላቅ እድሎችንና ስኬቶችን ይዞ እንደሚመጣም ያላቸውን ምኞት መግለጻቸውን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ቻድ፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ላይቤሪያ፣ የመን እና ኩዌት ሌሎች የዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር አባል የሆኑ ሀገራት ናቸው። የዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር (World Boxing) የተቋቋመው እ.ኤ.አ. አፕሪል 2023 ነው። ማህበሩ በአዲስ መልክ የተቋቋመው የቀድሞው ዓለም አቀፍ የቦክስ ማህበር (IBA) የአሰራር እና የሙስና ችግሮች ስለነበሩበት፣ ቦክስ በኦሊምፒክ ስፖርትነት የመቀጠል እድሉን ለማስጠበቅ በሚል ዓላማ ነው። ዋና መስሪያ ቤቱን በስዊዘርላንድ ያደረገው የዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር (World Boxing) ዛሬ አባልነታቸው ተቀባይነት ያገኙትን ጨምሮ 168 አባል ሀገራት በስሩ ይዟል።
ኢትዮጵያ በአለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና 6 ሜዳልያዎችን በማግኘት ውድድሯን አጠናቀቀች
Aug 10, 2026 194
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአሜሪካ ኦሪገን በተካሄደው የአለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና 6 ሜዳልያዎችን በማግኘት ውድድሯን አጠናቀቃላች። ትናንት እኩለ ሌሊት ላይ በተደረጉ የመጨረሻው ዕለት መርሃግብር በሁለቱም ፆታ በ1500 ሜትር ርቀት የተሳተፈችው ኢትዮጵያ ሜዳልያ ውስጥ መግባት አልቻለችም። በሴቶች ኤልሳቤት አማረ 4ኛ ፣ ሀረገወይን ካላዩ 9ኛ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።በወንዶች ደስታው ታዴ 12ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቅ ችሏል። ኢትዮጵያ በአጠቃላይ 2 ወርቅ ፣ 3 ብር እና 1 ነሐስ አሳክታለች። ከሁለት ዓመት በፊት በፔሩ ሊማ በተደረገው ተመሳሳይ ውድድር ኢትዮጵያ 6 የወርቅ ጨምሮ በአጠቃላይ 10 ሜዳልያ በማግኘት ማጠናቀቋ ይታወሳል። የዘንድሮውን ውድድር አዘጋጇ አሜሪካ 24 ሜዳልያዎችን በመሰብሰብ በበላይነት አጠናቃለች። ኬንያ በ11 ሜዳልያ 2ኛ ሆናለች ፤ ኢትዮጵያ ከዓለም 5ኛ ከአፍሪካ ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን አጠናቃለች።
የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች የወጣቶችን ስብእና የመገንባት ሚና አላቸው
Aug 9, 2026 266
ደብረ ብርሃን፤ ነሐሴ 3/2018(ኢዜአ)፡-የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች የወጣቶችን ስብእና ለመገንባት ሚና እንዳላቸው የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ውድድርን ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ አስጀምሯል።   የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ በዚህ ወቅት እንደገለጹት ከተማዋን የቱሪዝም፣ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ማእከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው። በተለይም የስፖርት ዘርፉን በማሳደግ ጤናማና አምራች ዜጋ ለማፍራትና በሀገር እና ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ወጣቶችን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።   ከተማ አስተዳደሩም ባለሀብቱንና ማህበረሰቡን በማስተባበር በየጊዜው የሚካሄዱ የታዳጊዎች ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድርን በልዩ ትኩረት እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል። በክረምት ወቅት ወጣቶች ገዜያቸውን የሚያሳልፉበትን ስፖርታዊ ውድድር ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ የተጀመረው ውድድርም የዚህ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ተክለዮሐንስ ኃይለጊዮርጊስ በበኩላቸው የክረምት ስፖርታዊ ስልጠናና ውድድሮች ታዳጊዎች የእረፍት ጊዜያቸውን በአልባሌ ስፍራ እንዳያሳልፉ ለማድረግ ታስቦ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።   ዛሬ በተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች እግር ኳስ ውድድር በ60 ቡድኖች የታቀፉ 1ሺህ 500 ስፖርተኞችን በማሳተፍ የሚካሄድ መሆኑን ገልጸዋል። የውድድሩ ዓላማ ወጣቶች በስፖርታዊ ስነ ምግባር ከመታነጽ ባለፈ ተሰጧቸውን አውጥተው በማሳየት በቀጣይ ለትልልቅ ክለቦች የሚመረጡበትን እድል የሚከፍት ነው ብለዋል። በተለይም ስፖርት ለሰላምና ለአንድነት ያለውን አበርክቶ በመጠቀም ወጣቶች አንድነታቸውን በማጠናከር ለአካባቢያቸው ሰላምና ልማት በጋራ እንዲሰለፉ ለማድረግ እንደሚካሄድ አስረድተዋል። "የኮኮብ እግር ኳስ ቡድን" አሰልጣኝ ሐብታሙ መለሰ፣ የክረምት ውድድር መዘጋጀቱ ታዳጊዎች በስልጠና ያገኙትን የቴክኒክ እውቀት በተግባር የሚያሳዩበት ዕድል ይፈጥርላቸዋል ብለዋል። "የአንድነት እግር ኳስ ቡድን" አሰልጣኝ ታምራት ደስታ በበኩላቸው ውድድሩ የባህል ልውውጥ በማድረግ አንድነትንና መተሳሰብን ለማጎልበት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል በደብረ ብርሃን ከተማ ዛሬ የተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ውድድር ለአንድ ወር የሚካሄድ መሆኑ ተመላክቷል።  
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተከላ፣ክትትልና የፅድቀት መጠን በጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ እየተረጋገጠ ነው
Aug 10, 2026 159
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፦የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተከላ፣ ክትትልና የፅድቀት መጠን በጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ እየተረጋገጠ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በኢንስቲትዩቱ የካርታ ስራ መሪ ስራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ካሳሁን ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በሳይንሳዊ የጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ፣በጂፒኤስ (GPS) ልኬትና በሳተላይት ምስል ትንተና መደገፍ መጀመሩ በመረጃዎች ጥራትና በውጤታማነት በኩል ከፍተኛ ለውጥ አምጥቷል። የጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ በዋናነት የመረጃዎችን የት፣እንዴት እና መቼ የሚሉ ሶስት መሰረታዊ ጥያቄዎች በትክክል መመለስ እንደሚረዳ ተናግረዋል። እንደ አቶ ቴዎድሮስ ማብራሪያ፣በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ችግኝ የሚተከልባቸው ቦታዎች በጂፒኤስ ንባብ አማካኝነት መጋጠሚያቸው ተለይቶ የተመዘገቡና ያልተመዘገቡ ተብለው ይከፈላሉ። በቅርቡ በተካሄደው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ብቻ ከ291 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ሙሉ በሙሉ በጂፒኤስ ተለክቶና የቦታ ስፋቱ ተሰልቶ መደራጀቱን ጠቁመዋል። ይህ አሰራር ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ የመረጃ መደጋገሞችንና የመረጃዎች መሳሳትን ሙሉ በሙሉ ማስቀረቱን ገልፀዋል። አሁን ተግባራዊ በተደረገው አሰራር መረጃው ቢሮ እንደደረሰ በሳተላይት ምስል እንደሚረጋገጥ ጠቁመው፤ በተመረጡ ቦታዎች ላይ ባለሙያዎች በአካል በመገኘት የማረጋገጥ ስራ እንዲሰሩ ተደርጓል ብለዋል። ችግኝ መትከል ብቻውን ግብ አለመሆኑን በመግለጽ፣የተተከሉ ችግኞች ማደጋቸውንና የአካባቢውን አረንጓዴነት መለወጣቸውን ለመከታተል የርቀት ቴክኖሎጂ (Remote Sensing) ትንተና ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። ባለሙያዎች የደረቅ ወቅት የሳተላይት ምስሎችን በመጠቀም የመሬት ሽፋኑን (የከተማ፣ የእርሻ፣ የወንዝ እና የደን) የሪፍሌክታንስ (Reflectance) ዋጋ በመተንተን ትክክለኛውን የደን ሽፋን እንዲለዩ ይደረጋል ብለዋል። በዚህ ሳይንሳዊ መንገድ በተካሄደው ዳሰሳና በመስክ ማረጋገጫ ስራ፣ ቀደም ሲል 17 በመቶ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን በአሁኑ ወቅት ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማደጉ መረጋገጡን ገልጸዋል። ይህ ትልቅ ስኬት የተገኘው ህብረተሰቡ ባለፉት ስምንት ዓመታት ባደረገው ያልተቋረጠ ጥረትና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በተከናወኑ ስራዎች መሆኑንም አመላክተዋል። በአሁኑ ወቅት ኢንስቲትዩቱ ያዘጋጃቸውን የደን፣ የሰብልና የከተማ መረጃ ክትትልን ጨምሮ 10 ማዕከላትን በመጠቀም መረጃዎችን ለውሳኔ ሰጪዎችና ለግብርና ሚኒስቴር ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ አስችለዋል
Aug 8, 2026 157
ጂግጂጋ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ አስችለዋል። 3ኛው ዙር የአካባቢ ብክለት መከላከል ክልል አቀፍ ንቅናቄ ''ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ'' በሚል መሪ ሐሳብ በጂግጂጋ ተካሄዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን እንደገለጹት፣ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሮች ምቹ አካባቢን በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ አስችለዋል። ጽዱ ኢትዮጵያን እውን ለማድረግም የፕላስቲክ ነክ ተረፈ ምርቶችን፣ የደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ብክለትን በመከላከል በውሃ እና አፈር ላይ እየተፈጠረ ያለውን ተጽዕኖ ለመቀነስ የወጡ ህጎችና መመሪያዎችን ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም የቆሻሻ ማስወገጃ ዘላቂ ሥርዓቶችን በመገንባት ከተሞች ምቹና ጽዱ እንዲሆኑ በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የአከባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ በበኩላቸው፣ መርሃ ግብሩ ባለፉት ሁለት ዙሮች የተገኙ ውጤቶችን በማጠናከርና፣ በማስፋት፣ ጤናማና ንጹህ አካባቢን የመፍጠር ተግባሩን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን አመልከተዋል። ''እንዲሁም አካባቢያችንን ለመጠበቅ እና ለመጪው ትውልድ ፅዱ ኢትዮጵያን ለማውረስ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ ለማረጋገጥም ጭምር ነው'' ብለዋል። 3ኛው ዙር የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ በቀጣዮቹ ሶስት ወራት የሚተገበርና በዋናነት የፕላስቲክ ብክለትን በመከላከል፣ አደገኛ ኬሚካሎችንና ቆሻሻዎች አያያዝን፣ እንዲሁም የድምፅ ብክለትን የመከላከል ተግባራት እንደሚከናወንም አክለዋል። እንደ ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ ገለጻ፤ ፅዱ ኢትዮጵያ በመንግስት ብቻ የሚከወን ባለመሆኑ በየቤታችን፣ በየትምህርት ቤቱ፣ በየመሥሪያ ቤቱና በፋብሪካዎች የምንፈጽማቸው በጎ ተግባራት ተደምረው ትልቅ ሀገራዊ ለውጥ ያመጣሉ። በዚህም ሁሉም የመንግስት ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የሴቶችና የወጣቶች ማህበራት እንዲሁም እያንዳንዱ ዜጋ የዚህ ሀገራዊ ንቅናቄ ባለቤት በመሆን በንቃት እንዲሳተፍም ጥሪ አቅርበዋል። የሶማሌ ክልል የአካባቢ ጥበቃና ገጠር መሬት አስተዳድር ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ሙህየዲን አብዲ በበኩላቸው በክልሉ ባለፉት ዓመታት በጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄዎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ጽዱ አካባቢ ለመፍጠር እየተከናወኑ የሚገኙ በርካታ ተግባራትም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የቢሮ ኃላፊው አረጋግጠዋል። በመርሃ ግብሩም በክልሉ ፕላስቲክን በመከላከል፣ መመሪያዎችን በመተግበርና ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ውጤታማ የሆኑ ከተሞች የእውቅና መስጠት ሥነ-ሥርዓት ተካሄዷል።
አረንጓዴ አሻራ ለትውልድ የሚተላለፍ ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃ ባህል ነው
Aug 8, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያውያን ለትውልድ የሚያስተላልፉት ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃ ባህል ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎት ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ገለጹ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ሃላፊዎችና ሠራተኞች፣ ’’ተስፋን እንትከል’’ በሚል መሪ ቃል በእንጦጦ ሸገር ፓርክ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አከናውነዋል።   የባንኩ የኮርፖሬት አገልግሎት ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ አረንጓዴ አሻራ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮችን መቋቋም ያስችላል። በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ስራዎች የታዩ ተጨባጭ ለውጦች መኖራቸውን አንስተው፣ በተለይም ለአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። የተፈጥሮ ስነ ምህዳሯ የተጠበቀና አረንጓዴ አገርን ለቀጣይ ትውልድ ለማስረከብ ችግኝ መትከልና መንከባከብ ወሳኝ ሀገራዊ ሀላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ ባንኩ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ250 ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን ገልጸው፤አረንጓዴ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ጠንካራ የኢትዮጵያዊያን የአካባቢ ጥበቃ ባህል መሆኑን ተናግረዋል። የባንኩ አመራሮች እና ሰራተኞችም በዚህ ታላቅ ሀገራዊ መርሀግብር የሚያደርጉትን ተሳትፎ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የህዝብን አቅም በማስተባበር የተከናወነ ታሪካዊ ስኬት ነው
Aug 7, 2026 233
ጅማ ፤ ነሃሴ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በመደመር መንግስት እሳቤ የህዝብ አቅምን በማስተባበር የተከናወነ ታሪካዊ ስኬት መሆኑን የጅማ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። የመደመር መንግሥት የተበታተነን አቅም በማቀናጀትና የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ በማጎልበት፣ በአንድ ቀን ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን መትከልን የመሰሉ በተግባር የተገለፁና የሚገለፁ እውነታዎችን የያዘ እሳቤ ነው። ይህም የኢትዮጵያውያን በጋራ መቆም፣ የውስጥ አቅምን አሟጦ መጠቀም እና የትብብር ባህልን ማሳደግ አዎንታዊ ለውጥ ለማምጣት እንደሚያስችል በተግባር ያረጋገጠና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጉዞ የሚያፋጥን ነው። ምሁራኑ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት እንደገለፁት፤ የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በመደመር መንግሥት እሳቤ የሕዝብ አቅምን በማስተባበር የተከናወነ ታሪካዊ ስኬት ነው። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ጥናት ትምህርት ክፍል መምህር ጌታቸው ጥላሁን (ዶ/ር) ፤ የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በመደመር መንግሥት እሳቤ የሕዝብ አቅምን በማስተባበር የተከናወነ ታሪካዊ ስኬት ነው ብለዋል። ይህንንም ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ለሀገራዊ ጥሪው ስኬት የድርሻውን በመወጣት ማሳየቱን ተናግረው ከመንግሥት ጎን በመቆምም ለኢኮኖሚው ዕድገት ያለውን ቁርጠኝነት መግለፁን ጠቁመዋል። ሕዝቡ በአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ያሳየውን የተቀናጀ መረዳዳትና ከፍተኛ ተሳትፎ፣ በሀገር ግንባታ፣ በኢኮኖሚ ዕድገት እንዲሁም በሕብረተሰብ አቀፍ በጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ ማስቀጠል የሚገባው መሆኑን አስረድተዋል። ባለፉት ዓመታት እየጎለበቱ የመጡትን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና የማዕድ የማጋራት እንቅስቃሴዎችን በምሳሌነት የጠቀሱት ምሁሩ፤ በጥቂቱ ታስቦ የተጀመረው ሥራ ትልቅ ደረጃ መድረስ እንደሚችል ማሳያ ነው ብለዋል። በተለይም በሁሉም ዘርፎች የተጀመሩ ዘላቂ የልማት ስራዎችን ከዳር ለማድረስ የዜጎች ሕብረትና አንድነት ወሳኝ መሆኑን የጠቆሙት ምሁሩ፤ ይህ የሕዝቡ ቀናነትና ለልማት የመቆም ባህል በሁሉም መስክ ሊስፋፋ እንደሚገባም አመልክተዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ሥነ-ምግብ መምህርና ተመራማሪ ዋሲሁን ሀሰን (ዶ/ር)፤ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ትልቅ ሀገራዊ ድል በመሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን በጋራ በመቆም የተቀዳጁትን የዓድዋን ድል የሚያስታውስ ነው ብለዋል። ሕዝባዊ ትብብርና መግባባት በሚገባ ከተፈጠረ በተሰማሩበት የሥራ ዘርፍ የሚፈለገውን ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ገልፀው ይህንንም ለሀገር ዕድገትና ብልፅግና ማዋል እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ ታስተናግዳለች
Aug 5, 2026 469
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ነው። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ መሠረት፣ ስብስባው የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው። የ47ቱ የአፍሪካ ቀጣና አባል አገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ለጋሾችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በስብስባው ላይ ይሳተፋሉ። የስብሰባው ተሳታፊዎች በቀጣናዊ የጤና አቅዶች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን የሚገመግሙ ሲሆን በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና የውሳኔ ሀሳቦች ላይ ይመክራሉ። እንዲሁም የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር፣ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የጤና ደህንነትን ለማሻሻልና የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሚረዱ የጋራ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካሶሎ፤ ስብሰባው አባል አገራት የቀጣናውን የጤና አጀንዳ እንዲቀርጹ፣ አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በመላው አፍሪካ ጤናማ፣ አስተማማኝና ጠንካራ ማህበረሰቦችን የመገንባት ሂደት ለማፋጠን ትልቅ እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። ተወካዩ አክለውም የኢትዮጵያ ስብሰባውን ማስተናገድ፤ ለቀጣናዊ ወንድማማችነትና ለጋራ ትብብር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ስኬቶች፣ በተለይም መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን በማስፋፋትና በቅርቡ በክልል የተከሰተውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በመቆጣጠር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳየት ዕድል እንደሚፈጥር መረጃው አመልክቷል። ስብስባው የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። በስብስባው ላይ የቴክኒክ ውይይቶች፣ አውደ ርዕዮች ፣ የሁለትዮሽ ስብሰባዎችና የሕዝብ ግንኙነት ስራዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በአፍሪካ ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ የፈጠራ ስራዎችንና የእውቀት ልውውጥን የሚያጎሉ እንደሚሆኑ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ የቀጣናዊ ጽሕፈት ቤቱ የበላይ አካል ሲሆን፤ በየዓመቱ በመሰብሰብ የቀጣናውን የጤና ፖሊሲ ይወስናል፣ የድርጅቱን ሥራዎች ይገመግማል፣ እንዲሁም በመላው አህጉሪቱ ለሚከናወኑ የጤና ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አጀንዳዎች ያስቀምጣል።
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች ነው- ሲኤንኤን
Aug 4, 2026 488
የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ኮረብቶች ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት መመልከቷን ተናግራለች። በዘገባዋ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ የሃይል ሚዛን መሆን እንደምትፈልግ ገልጻ፤በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ውስጥ በዋናነት የሚጠቅስ መሆኑን ተናግራለች። በምዕራብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከለበሱት ከፍተኛ የኮረብታ ስፍራዎች ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚያስገኙ ከፍተኛ የወርቅ ሀብቶች እንዳሉ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ብቅ እያሉ መሆኑን ትናገራለች። በሺዎች የሚቆጠሩ የግንባታ ባለሙያዎች እና ማዕድን አውጪዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ የሆነውን የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ ግንባታ እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጻለች። በስፍራው የሚገኙ የማዕድን እና ጂኦሎጂ ባለሙያዎች የወርቅ ማዕድኑን የማጣራት ስራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጻለች። ጋዜጠኛዋ የወርቅ ማጣራት እና ምርት ሂደቱን በተመለከተ ከባለሙያዎች ማብራሪያ ማግኘቷንም አመልክታለች።   ወርቁን የማግኘት ሂደቱ እጅጉን ፈታኝ እና አድካሚ እንደሆነ ገልጻ፥ይሁንና ልፋቱ ትልቅ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑን ተናግራለች። የወርቁን ግብአት ውጪ ሀገር ልኮ ከማጣራት ይልቅ በኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፋብሪካ የራሱ ማጣሪያ ፕላንት እንዳለው በጉብኝቷ ወቅት መረዳቷን አመልክታለች። የሲኤንኤኗ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ ወርቅ የሀገሪቷ ዋና የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጻለች። ባለፈው ዓመት በወርቅ የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ መሆኑን ተናግራለች። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ውጥኖች በግልጽ የሚያሳይና ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን ቀጣዩ የኢኮኖሚዋ ምሰሶ እያደረገች እንደምትገኝ ሲኤንኤን በዘገባው አስረድቷል።
የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር ይገባል
Jul 30, 2026 779
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018 (ኢዜአ)፦የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተትን ለመቋቋም አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ፡፡ የአፍሪካ ህብረት በፓሲፊክ ውቅያኖስ ሙቀት የሚፈጠር የአየር ንብረት መዛባት (ኤልኒኖ) አስመልክቶ አስቸኳይ ስብስባውን ዛሬ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል። በህብረቱ የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ውሃ እና ከባቢ አየር (ADREE) ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ የተዘጋጀው ስብሰባ እ.አ.አ በ2026 ይከሰታል ተብሎ የሚጠበቀውን የኤልኒኖ አየር ንብረት ክስተት ለመቋቋም እና አህጉራዊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከርን ያለመ ነው። ከፍተኛ የምክክር መድረኩ "የአፍሪካን ቅድመ ዝግጅት፣ የመቋቋም አቅም እና የአየር ንብረት እርምጃዎችን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ በአካል ከተገኙት ተሳታፊዎች በተጨማሪ በበይነ መረብ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሁነቱ ላይ ታድመዋል። የስብሰባው ዋና ትኩረት አፍሪካ ለኤልኒኖ የተቀናጀ ምላሽ እንድትሰጥ የጋራ ትብብርን መፍጠር ነው። በተጨማሪም በ31ኛው እና በ32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች (COP31) እና (COP32) ላይ የአፍሪካን ሚና ማሳደግ እና የአህሪቷን አጀንዳዎች ጎልተው እንዲታዩ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ይመክራል። ለአንድ ቀን የሚቆየው ስብስባ በባለሙያዎች እና በሚኒስትሮች ደረጃ ተከፍሎ ይካሄዳል። የአፍሪካ የሜቲዎሮሎጂ ትግበራዎች ልማት ማዕከል (ACMAD) የኤልኒኖ ክስተትን ትንበያ እና በአህጉሪቱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀርባል። በተጨማሪም በአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን መሪነት አህጉሪቱ በመጪዎቹ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች የምታደርገው ተሳትፎ እና ለዓለም አቀፉ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ጉባኤ የሚደረጉ ዝግጅቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። የአፍሪካ የውሃ ሚኒስትሮች ምክር ቤትም (AMCOW) ከ 2026 የአፍሪካ ህብረት የዓመቱ መሪ ሀሳብ ጋር የተያያዘ ሪፖርት ያቀርባል። የአባል ሀገራት ሚኒስትሮችም ስለ ኤልኒኖ ተፅዕኖ እና አህጉራዊ ምላሽ መግለጫዎችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው በኤልኒኖ ዙሪያ የተዘጋጀውን የድርጊት መርሃ ግብር፣ የባለሙያዎች ሪፖርት እና የጋራ የአቋም መግለጫ እንደሚያፀድቅም ተመላክቷል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተጨማሪ የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተዋል። ኤልኒኖ (El Nino) በፓሲፊክ ውቅያኖስ የውሃ ሙቀት ከመደበኛው በላይ በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ዓለም አቀፋዊ የከባቢ አየርና የአየር ንብረት መዛባት ክስተት ነው። የኤልኒኖ ተጽእኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተለመደ የከፋ ድርቅን፣ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋንና የሙቀት መጠን መጨመርን በማስከተል በግብርና እና በሰዎች ሕይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ሀገራት የአፍሪካ ህብረትን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል - አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና
Jul 29, 2026 1262
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርጉ የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው እና የህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት 49ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተጠናቋል። የምክር ቤቱ ስብሰባ “ ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚለው የ2026 የህብረቱ ዓመታዊ መሪ ሀሳብ አማካኝነት ተከናውኗል። የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ምክር ቤቱ አጀንዳ 2063 እና የህብረቱ መሪ ሀሳብን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል። የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የእርስ በእርስ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አመልክተዋል። በፓን አፍሪካኒዝም መንፈስ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ያሳዩት ፍላጎት አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ በበጎ ፈቃደኝነት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይፋ ማድረጋቸው የፋይናንስ ነጻነትን ማረጋገጥ የሚያስችል እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ሌሎች የህብረቱ አባል ሀገራት የኢትዮጵያንና የኬንያን ፈለግ በመከተል ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። ሀገራት የገቧቸውን ቃል ኪዳኖችና ስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መተግበር እንዳለባቸውም ነው ያስገነዘቡት። ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ለሚኒስትሮችና ሌሎች ልዑካን ላደረገችው አቀባበልም አመስግነዋል።
ሐተታዎች
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር!
Aug 9, 2026 438
ለብዙዎች ብርሃን የፈነጠቀው የገጠር ሞዴል መንደር! በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን ) የገጠሩ ማህበረሰብ የጨለማ ኑሮ የተፈረደበት ይመስል ኑሮውን ማሻሻል ሳይችል እልፍ ዓመታት ተቆጥረዋል፤ ለዘመናት መብራትና ውኃ ለማግኘትና ከቴክኖሎጂ ጋር ተቀራርቦ ለመኖር ወደ ከተማ መሰደድ ብቸኛው አማራጭም ነበር። የከተሜው ዋልታ የሀገር ኢኮኖሚ መሠረት የሚወሰንበት የአራሹ ገበሬ የኑሮ ደረጃ ባህላዊውን የአኗኗር ዘዬ ባለመልቀቁ ደስተኛ ጊዜ የሚያሳልፍበት ሂደት አድካሚ እንደሚሆን ግልጽ ነው። የገጠሬው የተበታተነ የአኗኗር ሥርዓትም ለገጠሬው አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፤ የእዚህን የህብረተሰብ ክፍል ምርቱን እንጂ ኑሮውን የጠየቀ አልነበረም ቢባል ግነት አይሆንም።   ቀደም ሲል በነበሩ መንግስታት ከተማን እንጂ ገጠርን ማዘመን የሚያስብ ስለመኖሩ ያጠራጥራል፤ ይህም በሀገሪቱ ለኢፍትሐዊ ዕድገት የራሱን ተጽዕኖ ሲያሳደር ቆይቷል። የመደመር መንግሥት ግን ይህን ቀይሮታል። ሀገር የመምራት ኃላፊነት ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ በከተማና በገጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ በዜጎች የኑሮ ሥርዓት ላይ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርጎ እየሰራ ነው ከተሜነት ብቻውን አድጎ የገጠሩ ማኅበረሰብ በቀድሞ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሆነ የተሟላ ዕድገት ማምጣት አይቻልም የሚል ጽኑ እምነት አለው። በእዚህም ከተማና ገጠርን ለማቀራረብ በገጠር ትራንስፎርሜሽንን የተለያዩ ኢኒሼቲቮችን ቀርጾ መተግበር ከጀመረ ከራርሟል። የገጠር ትራንስፎርሜሽን አንዱ አካል የሆነው የገጠር ሞዴል መንደር በአርሶ አደሮች ዘንድ የሚጨበጥ ተስፋን ይዘው ከመጡ ኢኒሼቲቮች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው። ከተስፋ ተሻግረው በዚህ ሞዴል መንደር የነዋሪነት ዕድልን ያገኙት ደግሞ ብርሃን አይተዋል፤ የትናት አኗኗራቸውን የቀየረ አዲስ ዛሬን በእጃቸው አድርገዋል፤ ነገን አልቀው መመልከት የግብርና ተግባራቸው አንዱ አካል ሆኗል። በአዲሱ መንደራቸው ዛሬ የሚያፈስ ቤት የለም፣ የእንስሳት ቆሻሻ ሽታ በአፍንጫቸው አይገባም፣ በሚቆረቁር እንጨት ወይም መደብ ላይ አይቀመጡም፤ የከተሜው መዘነጫ ሶፋ በሳሎናቸው ተከስቷል። ጓሮዎቻቸው ሁሉ ሙሉ እንደሆኑ አፍ አውጥተው የሚያወሩ ናቸው። በዚህ ቆስጣ፤ በዛ በኩል ጎመንና ቀይስር፤ ዘውር ሲሉ ደግሞ ከአስር የሚልቁ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፤ በአንድ ክፍል ደግሞ እናት ላም ከጥጃዋ ጋራ፣ የእንቁላል ዶሮ ከሥጋ ዶሮ ጋር ሁሉንም በአንድ ጊቢ ውስጥ ያገኛሉ። ምን ይሄ ብቻ አቮካዶ እና ፓፓያ፣ ሙዝና እንሰት፣ በርበሬና ሽንኩርት ሳይቀር ለተትረፈረፈ የአርሶ አደር ማዕድና ገበያ ራሳቸውን አዘጋጅተዋል።   አርሶ አደር ኃይሉ ሞትንሞስ በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የጌሊት ሞዴል መንደር ነዋሪ ናቸው። እርሳቸው "መንግስት ጨለማችንን ገፎ ብርሃን አሳየን" ሲሉ በጠንካራ ቃላት የገጠር ሞዴል መንደር ፕሮጀክት ያመጣላቸውን በጎ ነገር ይገልጻሉ። እውነት ነው ያላዩትን ብዙ ነገር አሳይቷቸዋል። ያም ብርሃን ቤት ውስጥ የሚበራ ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው፣ በነገ ተስፋቸውና በኢኮኖሚያቸው ላይ የፈነጠቀ ብርሃን ነው። ዛሬ ያሉበትን ህይወትም "ለእኔ አዲስ ነገር ነው። አይቼው አላውቅም፤ መቼም በራሴ ሀሳብ አላደርገውም ነበር።" ሲሉ ይገልጻሉ። መንግስት አበራልኝ ያልኩት በእጄ ያለኝን ያላየሁትን ዕድል ስላሳየኝ ነው በማለትም ሀሳባቸውን ይቀጥላሉ። እኛ ሀብት አለን፤ ሀብታችንን የምንጠቀምበት መንገድ ግን ትክክል አይደለም። ይልቁንም የምናባክነው ይበዛል በማለትም የቀደመ ሕይወታቸውን እያሰቡ ይቆጫሉ። አሁን ግን ብዙ ተገነዘብኩ የሚያስብል የመደመር መንግስት በመኖሩ አዲስ ሕይወት በአዲስ ተስፋ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። እርግጥ ነው የገጠር ሞዴል መንደር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ነው። ለአብነትም የማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ መሠረተ ልማት ዝርጋታን ማንሳት ይቻላል። የተሠሩ ሞዴል መንደሮች በመጀመሪያ የመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ የመሆን ዕድል ገጥሟቸዋል። በመቀጠል ንጽሕናው ያልተረጋገጠ የመጠጥ ውኃ ወንዝ ወርዶ ከመቅዳት ተቆጥበው በመንደራቸው የተገነባውን የከረሰ ምንድር ውሃ ከቧንቧ ቀድተው መጠጣት አስችሏቸዋል። በእሳት እና ኩራዝ ጭስ ሲሰቃዩ የነበሩ ዓይኖቻቸው ዛሬ ከሶላር ቴክኖሎጂ የመነጨ ብርሃን ማየት ጀምረዋል። ብርሃን ብቻ አይደለም ለወትሮ ለገበያ ወደ ከተማ ብቻ ሲወጡ ይመለከቱ የነበረውን ቴሌቪዥን ዛሬ በቤታቸው አስገብተው የመረጃና የመዝናኛ ዓለምን ተቀላቅለዋል። አርሶ አደሮቹ ቴሌቭዥንን ከመዝናኛነት ይበልጥ ለመረጃ እንደሚጠቀሙት ያነሳሉ። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን በዜና ተከታትሎ መረዳት፣ የገበያ ሁኔታን ማወቅ፣ የግብርና ሥራ ተሞክሮን መቅሰምና የአየር ንብረት ሁኔታን ጨምሮ ለሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙት ከቴሎቪዥን መስኮት እንደሆነ ይናገራሉ።   በጓሯቸው የተትረፈረፈ የሌማት ትሩፋት ምርት መሰብሰብ የሚያስችላቸው ምቹ ሁኔታ ደግሞ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ አለው። በተለይ መንግስት በጓሯቸው ጥምር እርሻ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ የነገ ኢኮኖሚያቸውን በአስተማማኝ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ ነው። ከተማን መናፈቅን ያስቀረው የገጠር ሞዴል መንደር ያኔ ከጅምሩ አመኔታን አላገኘም። የቦታና የአካባቢ ቁሳቁስ ለማቅረብ ዝግጁ እስካለመሆን የደረሱ አርሶ አደሮችም ነበሩ። በወቅቱ ጉዳዩን እንደፌዝ አዩት። ዛሬ ግን ውጤቱን በአግራሞት በዐይናቸው ተመለከቱ። የተናገረውን የሚከውን፤ የጀመረውን የሚጨርስ የመደመር መንግሥትን ተጨባጭ ስራዎች በማረጋገጥ እንደ ትንግርት ቆጠሩ። ዛሬ በየአካባቢው ያሉ አርሶ አደሮች በቁጭት ተሞልተው መንደራቸውን ወደዚህ የሞዴል መንደር እሳቤ ለመቀየር ተነሳስተዋል። የጌሊት ቀበሌ አርሶ አደሮቹ መኮንን አርዶ እና ነጻነት ተስፋሁን ለዚህ ተጠቃሾች ናቸው። ያዩትን ተሞክሮ በራስ አቅም በመንደራቸው ለማስፋፋት ማቀዳቸውን ተናግረዋል። ከተማ ሄደን የምናወጣውን ወጪና የምናባክነውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት እዚሁ መዝናናት የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ብለዋል።   "ይህ ዕድል ለእኛ ለአርሶ አደሮች በታሪክ የሚነገር ትልቅ አጋጣሚ ነውም" ይላሉ። በጤዛ እየራስን እንጓዝበት የነበረው መንገዳችን ዛሬ ሰፍቷል። ተሽከርካሪ በደጃችን ስለሚያልፍም ምቹ ዕድልን ይዞልን መጥቷል። ይህን ጅምር ተግባር ወደ ላቀ ውጤት ማሸጋገር የእኛ ድርሻ ነውና ጠንክረን እንሠራለንም ብለዋል።   ይህን ዕድል ወደ ትልቅ አቅም ለመቀየር መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳ የሸሸቃ ሞዴል መንደር ተጠቃሚ አርሶ አደር አልዓዛር ዘርክናንስ ናቸው። የዶሮና የከበት እርባታን እንዲሁም ዘመናዊ የንብ ማነብ ሥራን ከመደበኛው የእርሻ ሥራ ጋር አስተሳስረው በመሥራት ከቤተሰብ ፍጆታ ተርፎ ለገበያ የሚበቃ ምርት ለማምረት እየተዘጋጁ ነው።   ይህም የገቢ አቅማቸውን ከማሳደግ ባለፈ ልጆቻቸው ወተትና የወተት ተዋጽኦ በቤታቸው እንዲያገኙ ያደርጋል። ማር፣ እንቁላል እና ሥጋ እንዳያምራቸው የሚያደርግ ትልቅ ኢኒሼቲቭም ነው። አንዱ ቢጎድል በሌላው እየሞሉ የሚኖሩበትን የሥራ መስክ አጠናክረው ለውጤት አብቅተው ለተሻለ ለውጥ እንደሚሠሩ አክለዋል። የአርሶ አደር እናቶች ዘምቢል ይዘው አትክልትና ፍራፍሬ ሸመታ ወደ ገበያ ማቅናት የለባቸውም። ይልቁንም ከጎሮቸው ወደ ገበያ ይዞ መውጣት የኑሮ ዘዬያቸው ወግ ነው። ወይዘሮ መሠረት ማሞ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የበቆ ሞዴል መንደር ነዋሪ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ያልለመዱትን አዲስ ሕይወት ከአዲስ ተስፋ ጋር መጀመራቸውን ከሚናገሩት መካከል ናቸው።   ትናንት ኩሽናቸው፣ መኝታቸው እንዲሁም የከብትና የዶሮ ማደሪያ በአንድ ቤት ወስጥ የተወሰነ እንደነበር ያስታውሳሉ። ዛሬ ግን ሽንት ቤትና መታጠቢያ ቤት ሳይቀር ለየብቻ የራሱ የሆነ ቤት ተገንብቶ ጽዳቱ የተጠበቀ ኑሮ መኖር ጀምረዋል። ቤታቸው ሲገቡና ሲወጡ ለዓይን ማራኪ፤ ለመቀመጥ ምቹ፤ ለመተኛትም ንጹህና ወገብ የሚያሳርፍ ሆኖ አግኝተዋል። እናም በዚህ እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ። "መንግስት እንደ አባት ጎዶሏችንን ሞልቷል" ሲሉም ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት ይህ የአርሶ አደሮችን ሕይወት ብሩህ ያደረገው የገጠር ሞዴል መንደር ኢኒሼቲቭ በመላው ሀገሪቱ በመስፋፋት ላይ ነው። ባለፉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 16 ሞዴል መንደሮች በ16 ወረዳዎች ተገንብተዋል።   የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት ኢኒሺዬቲቩ የአርሶ አደር ኑሮ ዘዬን ከማሻሻል ባለፈ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ ጋር ለማቆራኘት ያስቻለ ነው። የተሻለ መኖሪያ ቤት ኖሮት በጓሮው የሚበላ ነገር ካጣ ሕይወቱ ትርጉም ያለው ለውጥ አያመጣም። ይህም በመሆኑ ቤቶቹን ከእያንዳንዱ የግብርና ልማት ዘርፎች ጋር በማጣመር እንዲገነቡ የተደረገው። ይህም የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል ሀገራዊ ስትራቴጂን የሚያጠናክርና ገበያን የማረጋጋት ዓላማን የያዘ ጭምር ነው። በገጠር ሞዴል መንደር ግንባታ የተገኘው መልካም ውጤት በቀጣይ በሁሉም ወረዳዎች የሚስፋፋ ሲሆን በዞን እና ወረዳ መዋቅሮች ድጋፍና ክትትል በቀበሌ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል አንስተዋል። ይህ ኢኒሼቲቭ የሀገራዊ ብልጽግና ጉዞ አንዱ አቅም ነው። የተደመረ የማኅበረሰብ ብልጽግና ሀገርን ከፍ ያለ የዕድገት ማማ ላይ ያስቀምጣታል። እነሆ የክልሉ አርሶ አደሮች የአካባቢያቸውን ጸጋ ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ የሚቀይሩበት መስክ በሞዴል መንደር ምክንያት እጃቸው ላይ ደርሷል። አርሶ አደሮቹ እንዳሉትም በብዙ መንገድ ጨለማ የከበበው የገጠሩ ማኅበረሰብ ሕይወት ዛሬ ብርሃን ማየት ጀምሯል። ይህ የብርሃን ፋና እየተቀጣጠለ ወደ ብዙኃኑ ሊደርስ የሁሉንም ፍላጎት አነሳስቷል። ሥሩ ከማለት ይልቅ ሠርቶ ማሳየትን የሚያስቀድመው የመደመር መንግስት የፈጠራቸው የገጠር ሞዴል መንደሮች ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን በዘላቂነት የሚያሳምሩ ናቸው። ሰላም እንሰንብት!  
ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የአፍሪካ ኃያል ሀገር እየሆነች ነው-ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት
Aug 7, 2026 424
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 1/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሪነት የመጪው ዘመን የአፍሪካ ኃያል ሀገር ወደመሆን እየተሸጋገረች ነው ሲል ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት ዘግቧል። ፈርስት ፖስት ሚዲያ ኢትዮጵያን በተመለከተ በሠራው ትንታኔው የሰው ዘር መገኛ፣የጥንታዊ መንግስታት ምድር፣የንግድ መስመሮች እና ከፍ ያለ የአፍሪካ ታሪካዊ መሰረት ያላት ሀገር መሆኗን አውስቷል። ሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ከቀድሞ ገናና ታሪኳ እኩል ታላቅ የሆነ አዲስ ምዕራፍ ለመገንባት በትጋት ላይ መሆኗን አንስቷል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት በቀጣናው እና የአፍሪካ ኃያል ሀገር መሆን የሚያስችላትን እንዲሁም የአህጉሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚበይንና የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሠራች መሆኗንም እንዲሁ። ለረጅም ዓመታት ዓለም ኢትዮጵያን የሚያውቃት በጦርነት፣በድርቅ እና በፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንደነበር በማስታወስ፥ዛሬ ግን ሀገሪቱ ይህንን የተዛባ ትርክት በኢነርጂ መሠረተ ልማት፣ በአቪየሽን፣ በማዕድን እና በዲጂታል ኢኮኖሚ አስደማሚ ለውጦች ለመቀየር እየሠራች ነው ብሏል። ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ተሻግራ እንዴት በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት ካላቸው ኢኮኖሚዎች ቀዳሚዋ ሆና ልትቀጥል ቻለች? የሚለውን ጥያቄ በማንሳትም በዝርዝር መልሶቹን ያብራራል። የዚህ ዋና ጥያቄ ዝርዝር ምላሽ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት እየተተገበሩ የሚገኙ የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ ነው ያለው ሲል አንስቷል።   • የመጀመሪያው የኢነርጂ አብዮት እና ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ነው። በዚህ የኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ጎልቶ የሚነሳው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሲሆን፣ ከ5 ሺህ ሜጋዋት በላይ የማመንጨት አቅም ያለው የአፍሪካ ትልቁ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት መሆኑን ፈርስት ፖስት በዘገባው ጠቅሷል። ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መሻቶች መሰረት፣የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የውጭ ምንዛሬ እና የቀጣናዊ ተጽዕኖ መፍጠሪያ አቅም መሆኑንም አብራርቷል። የሕዳሴ ግድብ ልዩ የሚያደርገው የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ከዓለም ባንክ ወይም ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አንድ ሳንቲም ሳይበደር በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደም፣ ላብና ገንዘብ የተገነባ አፍሪካውያን በራሳቸው ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየነው ብሏል። ለኢትዮጵያውያን ግድቡ ከኮንክሪት እና ከተርባይን በላይ ትርጉም አለው ያለው ይህ የፈርስት ፖስት ዘገባ፥ እጅግ የላቀ እራስን የመቻል እና የኢኮኖሚ ነፃነት ማሳያ ሐውልት መሆኑንም ተንትኗል። ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን ለኬንያ፣ ለጂቡቲ እና ለሱዳን በመሸጥ ኤሌክትሪክን ወደ ከፍተኛ ገቢ ማመንጫነት እየቀየረች ከመሆኑም በላይ የመላው ምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የትስስር ማዕከል ሆናለች ነው ያለው። • የኢትዮጵያ የዕድገት ምሰሶ አቪዬሽን እና ቀጣናዊ ትስስር ኢነርጂ ብቻውን ኢኮኖሚያዊ አቅምን አይገነባም፤ ይልቁንም ኢነርጂ ኢንዱስትሪን ያነቃቃል፣ ትስስር ዓለም አቀፍ ንግድን ይመግባል ያለው ፈርስት ፖስት፥የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁን ለላቀ የዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ጉዞ መጀመሩን አንስቷል። በ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በየዓመቱ እስከ 110 ሚሊዮን ተጓዦችን እና ወደ 4 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ የዕቃ ጭነት ማስተናገድ አቅም አለው። ሙሉ በሙሉ ግንባታው ሲጠናቀቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከታላላቅ የአቪዬሽን ማዕከላት አንዱ ይሆናል ብሏል።   ይህ ፕሮጀክት የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማሲ መናኸሪያ የሆነችውን አዲስ አበባንና አፍሪካን፣ከሌሎች የዓለም ክፍሎች የሚያስተሳስር ዋና የመተላለፊያ ማዕከል እንደሚሆንም ተገልጿል። ስለዚህ አዲሱ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንት እና ለቱሪዝም፣ ለዓለም የዲፕሎሲ ትብብር ጉልህ ሚና እንዲያበረክት ታስቦ እየተገነባ ነው ብሏል። • የማዕድን ኢንቨስትመንትና በምግብ ራስን መቻል በሌላ በኩል ከኢትዮጵያ መሬት በታች ላለው የማዕድን ሀብቷ ትኩረት በመስጠት የልማት አብዮት እያካሄደች ስለመሆኑም ተንትኗል። ሀገሪቱ የወርቅና ሌሎች ማዕድናት ማውጫ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት አዳዲስ የውጭ ምንዛሬ ምንጮችን እያፈራች የማዕድን ኢንዱስትሪዋን እያሳደገች ነው። ወርቅ በፍጥነት ከኢትዮጵያ ቀዳሚ የወጪ ንግድ ምርቶች አንዱ በመሆን ለረጅም ጊዜ በግብርና ላይ ብቻ ጥገኛ ሆኖ የቆየውን ኢኮኖሚ ወደ ብዝኃ ዘርፍ እያሸጋገረ ይገኛል። በሌላ በኩል በምግብ ራስን ከመቻል ውጭ የትኛውም ኢኮኖሚያዊ ለውጥ የተሟላ ሊሆን አይችልም ያለው የፈረስት ፖስት ዘገባ፥ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆኑን ጠቅሷል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን እንድትችል በጀመረው የለውጥ ጉዞ አስደማሚ ውጤት እያመጣ ነው ብሏል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከጉባ ብስራቶች አንዱ የሆነውና በሶማሌ ክልል እየተገነባ የሚገኘው የማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት በየዓመቱ 3 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ ዩሪያ ማዳበሪያ ማምረት የሚችል ነው። ይህም ከውጭ የሚገባውን ማዳበሪያ ጥገኝነት በመቀነስ የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚያስችል አብራርቷል። "የምግብ ዋስትና የእኛ ስትራቴጂካዊ ጣልቃ ገብነት ነው።ያንን ግብ እውን ለማድረግ ግብአቶች ላይ መስራት አለብን።በግብአት ላይ መስራት ካልተቻለ የምግብ ዋስትናን እውን ለማድረግ መንገድ የለውም" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ በማካተት ዘገባው ሰፊ ሽፋን ሰጥቷል። ዲጂታላይዜሽን እና የኢንቨትመንትና የገበያ ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ለውጥ ወደ ዲጂታልም እየተሸጋገረ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እንደተናገሩት የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስልጠና ከዕቅዱ ቀድም ከመሳካቱም በላይ በርካታ ወጣቶች የዲጂታል እውቀት ባለቤት አድርጓል።   በተመሳሳይ የዲጂታል ትስስር እየሰፋ ሲሆን የ4ጂ እና 5ጂ አገልግሎቶች በበርካታ ከተሞች ተደራሽ ሆኗል። ኢትዮጵያ ለበርካታ አስርት ዓመታት ተዘግተው የቆዩ እንደ ቴሌኮሙኒኬሽን፣ ባንክ እና የካፒታል ገበያዎች ያሉ ዘርፎችን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረጓንም አድንቋል። የካፒታል ገበያን መጀመሯም የግል ካፒታል ልውውጥን በማጎልበት ለኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተንትኗል። እነዚህ ማሻሻያዎች በአጠቃላይ በመንግስት ቁጥጥር ስር ከነበረው የኢኮኖሚ ወደ ግል ዘርፍ ኢንቨስትመንት እያደገ የሚሄድ ኢኮኖሚ መሰረታዊ ለውጥን እየተገነባ መሆኑን ያሳያሉ ነው ያለው። ኢትዮጵያ ካላት የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ አኳያ እድልና ፈተናዎች ከፊቷ መሆናቸውን በማንሳት፥ አዲሱን የዓለም አቀፍ የትብብር ጥምረት ብሪክስ አባል መሆኗን አውስቷል። ከቻይና፣ ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት፣ ከምዕራባውያን አጋሮችና ከአፍሪካ ኢንቨስተሮች ኢንቨስትመንትን እየሳበች እንደምትገኝም እንዲሁ። ኢትዮጵያ ጎራ ሳትለይ ከሁሉም የዓለም ሀገራት ጋር ትብብሯን እያጠናከረች ነው ብሏል። ዓለም ኢትዮጵያን የምታስታውሰው በጦርነት ቢሆንም፥ኢትዮጵያ ዓለም በአዲሱ የለውጥና የስኬት ጉዞዋ እንዲያስታውሳት እየሠራች ነው። ለዚህም በመላው ሀገሪቱ በሁሉም ዘርፍ ግዙፍ የኢኮኖሚ ሽግግር እየተካሄደ ሲሆን፥ ይህ የኢትዮጵያ ጉዞ ለቀጣዮቹ ዓመታት የቀጣናውንና የአፍሪካን ኢኮኖሚያዊና አጠቃላይ ገጽታ በአዲስ መልኩ የሚቀርጽ ነው ሲል ፈርስት ፖስት ዘገባውን አብራርቷል።
ያቀደችውን በተግባር የምታሳካ ታላቅ ሀገር
Aug 3, 2026 741
የአንድ ሀገር ታላቅነት ከሚለካባቸው ጉዳዮች አንዱ የተያዙ ሀገራዊ እቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም ዋነኛው ነው። ኢትዮጵያም በዛሬው እለት በአንድ ጀምበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችው አዲስ ታሪካዊ ስኬት፣ ሀገሪቱ ያቀደችውን በተግባር ማሳየት የምትችልና ትልልቅ ህልሞችን የመተርጎም አቅም ያላት ታላቅ ሀገር መሆኗን ለመላው ዓለም በተግባር ያስመሰከረ ነው። ይህ በአንድ ጀምበር የተከናወነ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በርካታ ጥልቅ ትርጉሞችን የያዘ ነው፡ በአንድ ጀንበር ከ805 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ግዙፍ የሎጂስቲክስ፣ የዝግጅትና የህዝብ ንቅናቄ ስራን ይጠይቃል።   ይህ ስኬት ሀገሪቱ ማንኛውንም ታላቅ አገራዊ እቅድ አቅዳ እስከ መጨረሻው የትግበራ ምዕራፍ ድረስ በብቃት የመምራትና የማስተባበር ተቋማዊና ህዝባዊ አቅም እንዳላት ማረጋገጫ ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ዕድሜ፣ ጾታ፣ ወይም ልዩነት ሳይለያያቸው በአንድ ቀን ለተመሳሳይ አገራዊ ዓላማ መቆማቸው፣ ኢትዮጵያውያን ለጋራ እድገታቸውና ለሀገራቸው የወደፊት ተስፋ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎትና አንድነት አሳይቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት ዋና ስጋት በሆነበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ እርምጃ ለችግሩ መፍትሔ በመስጠት ረገድ የዓለም አቀፍ መሪነቷን ያስመሰከረችበት አጋጣሚም ጭምር ነው። ይህ ስኬት ሀገሪቱ የገጠሟትን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፈተናዎች ተሻግራ፣ አቅሟን አስተባብራ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ለዜጎቿም ሆነ ለውጭው ዓለም የሰጠችው ትልቅ የራስ መተማመንና የተስፋ መልእክት ነው። በአጠቃላይ፣ በአንድ ጀምበር የተከናወነው ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያ አርቆ የማሰብና የማቀድ ችሎታዋን ብቻ ሳይሆን፣ ያቀደችውንም በአንድነትና በቁርጠኝነት ወደ መሬት በማውረድ በተግባር የምታሳይ ታላቅ ሀገር መሆኗን በግልጽ ያረጋገጠ አኩሪ ተግባር ነው።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ ትንሳኤ ብስራት!!
Aug 2, 2026 549
በሐዊ አጫሉ መግቢያ፡- የኢንዱስትሪ ዘርፍ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬን ከሚወስኑ ዋነኛ የብልፅግና ማረጋገጫ ምሰሶዎች መካከል በግምባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ዘርፉ ምርትን ከማሳደግ ባሻገር የሥራ ዕድል ፈጠራን፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና የሀገር ውስጥ ምርታማነትን የሚያፋጥን የልማት ሞተር ነው። ኢትዮጵያም ከግብርና መሠረት የተነሳ ኢኮኖሚዋን ወደ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ሁሉን አቀፍ የምርት ሥርዓት ለማሸጋገር ከምታደርገው ጥረት መካከል ኢንዱስትሪውን በቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶነት በማካተት እየሰራችበት ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና ቴክኖሎጂ አምስት ዐበይት የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት ምሰሶዎች ተመሥርቶ እየተመራ ይገኛል። ከእነዚህ ውስጥ ኢንዱስትሪው የምርት አቅምን በማሳደግ የግብርና ምርቶችን ወደ ተጨማሪ እሴት በመቀየርና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ፋይዳ እያስገኘ ነው። ይህንን ሽግግር እውን ለማድረግ የምርት አቅምን ማሳደግ፣ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር፣ የአቅርቦት ሰንሰለትን ማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና የሰው ኃይል ልማት ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ የቀድሞ ገጽታ፤ ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ለውጥ መንገድ!! በቀደሙት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተለያዩ ዕድሎችንና ፈተናዎችን በማስተናገድ በርካታ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል። ሀገሪቱን ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር በተደረጉ ጥረቶች የተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተገንብተዋል። እነዚህ ፓርኮችም በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳና የቆዳ ውጤቶች እንዲሁም በግብርና ምርት ማቀነባበር ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የተሞከረበት ወሳኝ ምዕራፍ እንደነበር ይታወሳል። ይሁን እንጂ ይህ ጉዞ በበቂ መሠረተ ልማት፣ በተሟላ የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና በተቀናጀ የምርት ሰንሰለት እጥረት ምክንያት በበርካታ ፈተናዎች ለመውደቅ ተገዶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ውስንነት፣ ዕውቅትና ክህሎትን የተሰላበሰ የሰው ኃይል አለመኖር፣ የፋይናንስ እጥረት፣ ውስብስብና አስቸጋሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትና የገበያ ትስስር እጥረት የዘርፉን እድገት ገድበው የነበሩ ሁነኛ ተግዳሮቶች ናቸው። ከመዋቅራዊ ተግዳሮት ወደ ምርታማነት፤ የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የለውጥ ፍኖት!! ባለፉት ዓመታት በኢንዱስትሪ ዘርፉ የተስተዋሉ መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታትና የሀገሪቱን የማምረት አቅም ለማሳደግ አዳዲስ የለውጥ አቅጣጫዎች ተነድፈው ተተግበረዋል። በተለይም ኢንዱስትሪን ከተለመደው የምርት ሥርዓት በማሻገር ወደ ተወዳዳሪ ዘመናዊና ውጤታማ የማምረቻ ማዕከል ለመቀየር የተለያዩ የፖሊሲማሻሻያዎች ተደርገዋል። የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማሳደግ፣ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን ማስፋት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን፣ የሰው ኃይል አቅምን ማሳደግና የግብርና-ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር በዘርፉ የተወሰዱ ሁነኛ የለውጥ እርምጃዎች ናቸው። በዚህም የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነት በማጎልበት ከሀገር ውስጥ ገበያ እስከ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ድረስ ውጤት እያስገኘ ነው። የግል ባለሃብቱ ሚና፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሞተር!! የኢንዱስትሪ ልማት በመንግሥት ጥረት ብቻ የሚሳካ አይደለም። የግል ዘርፉ በካፒታል፣ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂና በአስተዳደር ብቃት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ለዘርፉ ዕድገት የማይተካ ሚና አለው። በዚህ ረገድ የግል ባለሃብቱ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ዋና አጋር እንዲሆን የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተሻሽለው እየተሰራባቸው ይገኛል። ይህም የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት በማሻሻል፣ የንግድ ሥራ ሂደቶችን በማቀላጠፍ፣ የፋይናንስ ተደራሽነትን ማስፋትና የምርት አቅምን በማሳደግ የግሉን ዘርፉ የምርታማነት አቅም እያጎለበተ ነው። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ የትንሳኤ ብስራት!! በሀገራችን የኢኮኖሚ አቅጣጫ ውስጥ የምርትና አገልግሎት አሰጣጥን በማቀናጀት አዲስ ምዕራፍ ከከፈቱ ዐበይት ሀገራዊ መርሃ-ግብሮች መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተጠቃሽ ነው። ይህም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ የማምረት ባህልን በማሳደግ ዘርፉ ወደ አዲስ የልማት ምዕራፍ የሚሸጋገርበት ሁነኛ ዕድልን ፈጥሯል። ንቅናቄው የማምረት አቅምን በማሳደግ ሥራ ያቆሙ ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ መመለስ፣ የአምራቾችን ችግሮች በፍጥነት መፍታትና አዳዲስ ባለሃብቶችን ወደ ዘርፉ በመሳብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤ እያበረከተም ይገኛል። በዚህ ሂደት በፋይናንስ፣ በግብዓት አቅርቦት፣ በውጭ ምንዛሬና በተቋማዊ ቅንጅት ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎች የአምራች ዘርፉን የምርታማነት አቅም በማጎልበት ጉልህ ሚና ተጫውቷል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲያንሰራራ በማድረግ የምርታማነት አብዮት እንዲቀጣጠል እያደረገ ይገኛል። የንቅናቄው ዋና ዓላማ በአምራች ዘርፉ የነበሩ ማነቆዎችን በመፍታት የኢትዮጵያን የማምረት አቅም ማሳደግ ነው። ይህም ሥራ ያቆሙ ወይም በአቅማቸው ልክ ያልሠሩ ፋብሪካዎችን ወደ ሙሉ ምርት በመመለስ የአምራቾችን ችግር በተቀናጀ መንገድ መፍታት፣ የፋይናንስና የግብዓት ተደራሽነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጓል። በዚህ ሂደት የማምረቻ ዘርፉ በአዲስ የሥራ ባህል፣ በተቋማዊ ቅንጅትና በፈጣን ውሳኔ አሰጣጥ እየተመራ መሆኑ የለውጡን ፍጥነት እያሳደገው ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ተደራሽነትን ማሻሻልና የምርት ጥራትን ማረጋገጥ የኢንዱስትሪው ትንሳኤ ዋና ማሳያዎች ናቸው። ለአብነትም፡- የፋይናንስ አቅምና የብድር አቅርቦት ማሻሻል፡- የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዋነኛ እንቅፋት የሆነውን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ በተደረገው ርብርብ፣ የብድር አቅም ቀደም ሲል ከነበረበት 40 ቢሊዮን ብር ወደ 115 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ለአምራቾች ሰፊ የካፒታል አቅም መፍጠር ተችሏል። የውጭ ምንዛሬ ግኝትና የግብዓት ድጋፍ ማደግ፡- ንቅናቄው ከመጀመሩ በፊት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ይቀርብ የነበረው የውጭ ምንዛሬ መጠን አሁን ላይ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንዲደርስ ተደርጓል። ይህም ፋብሪካዎች ከአቅማቸው በታች እንዲሠሩ ያስገድድ የነበረውን የምርት ውስንነት በከፍተኛ ደረጃ አቃሎታል። የምርት ዕድገት፣ ተኪ ምርትና የኤክስፖርት አፈጻጸም፡- ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ረገድ ከነበረበት 348 ሚሊዮን ዶላር ወደ 5.9 ቢሊዮን ዶላር በማደግ ግዙፍ ሀገራዊ ድል ተመዝግቧል። እንዲሁም በኤክስፖርት ገበያ የሚገኘው ገቢ ከ385 ሚሊዮን ዶላር ወደ 607 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ማለት ችሏል። ተቋማዊ ቅንጅትና አዲስ የሥራ ባህል ማዳበር፡- በክልሎችና በፌዴራል ተቋማት መካከል የነበረውን የቢሮክራሲ ጫና በመቀነስ ፈጣን ውሳኔዎች እንዲሰጡ መደረጉ፤ እንዲሁም ህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርትን በኩራት የመጠቀም እና የሀገር ፍቅር ስሜትን ከአምራችነት ጋር የማስተሳሰር ትልቅ ማህበራዊ ንቃተ-ህሊና መገንባት ተችሏል። የወደፊት ተስፋ፤ ኢትዮጵያ አዲሲቷ አፍሪካዊት የኢንዱስትሪ ምርታማነት ተምሳሌት ሀገር!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ በቀጣይ ዓመታት ከተለመደው ማምረት ወደ ዘመናዊ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የምርት ሥርዓት እንዲሸጋገር ይጠበቃል። የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሜሽን፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና የፈጠራ ሥርዓቶችን ወደ ማምረቻ ዘርፉ ማስገባት የወደፊቱ ትኩረት ይሆናል። በተመሳሳይም ጠንካራ የግብርናና ኢንዱስትሪ ትስስር፣ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት፣ ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአህጉራዊ ገበያ ተደራሽነት የሀገሪቱ ቀጣይ የኢንዱስትሪ ግቦች ናቸው። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) የሚፈጥረውን ሰፊ የገበያ ዕድል በመጠቀም ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል እንድትሆን የሚያስችል መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ማጠቃለያ፡- ማምረት፤ የኢትዮጵያ የብልፅግና ቁልፍ መሳሪያ!! የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ ከፈተና ወደ ዕድል፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል፣ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ተጨማሪ እሴት ያለው ምርት አቅራቢነት በማምራት እመርታዊ ውጤቶችን እያስገኘ ነው። የኢንዱስትሪውን አቅም ማሳደግ ማለት ፋብሪካዎችን ብቻ ማስፋፋት ሳይሆን የሀገርን ምርታማነት፣ የወጣቶችን ዕድል፣ የኢኮኖሚ ነፃነትንና የልማት ዘላቂነትን ማረጋገጥ ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን የዛሬ ልማት ብቻ ሳይሆን የነገውን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚገነባ ሀገራዊ ራዕይ ነው።  
ትንታኔዎች
ወዳጅነት ፓርክ ፦ የመደመር እሴት ማሳያ
Aug 11, 2026 53
በሙሴ መለሰ በአዲስ አበባ መሐል የሚገኘው የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት ስምንት ዓመታት ከተገነቡት የመጀመሪያዎቹ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች አንዱ ነው። ይህ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውና 56 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ባለው የ“ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት” (Beautifying Sheger Project) ስር የተከናወነ ነው። ፕሮጀክቱ በሁለት ዋና ዋና ምዕራፎች ተከፍሎ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ሊጠናቀቅ ችሏል። ኢትዮጵያ የጀመረችው ይህ የከተማ ውበትና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ የውበት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ሀብት ፈጣሪ መሆኑንም በተግባር ያረጋገጠ ህያው ማሳያ ነው። የወዳጅነት አደባባይ የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሂደት በ2011 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን፣ ቀደም ሲል የቆሻሻ ማጠራቀሚያና ክፍት ቦታ የነበረውን ስፍራ ወደ ዘመናዊ አረንጓዴ ሥነ-ምህዳር ለመቀየር ያለመ ነበር። ግንባታው በ11 ወራት ብቻ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ በጳጉሜ 2012 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በቀድሞዋ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት ሆኗል። ይህ ክፍል 32 ሄክታር መሬት በማልማት፣ አሳ እና ዳክዬዎች የሚቀዝፉበት ሰው ሠራሽ ሐይቅ፣ ትልቅ አደባባይ (Square)፣ እና 1 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻን መልሶ ማቋቋምን ያካተተ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ለምሽት መዝናኛ የሚሆን ማራኪ የፏፏቴ ላይ የብርሃን ትርኢት (Dancing Fountain)፣ ከ16 በላይ የውጪ ላይ ስብሰባ ማካሄጃ ቦታዎች (Event Venues)፣ የሰርግ አፀዶች፣ ካፌዎች፣ የፎቶ ስቱዲዮዎች እና ጠዋት ጠዋት የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ሩጫ ለማድረግ ምቹ የሆኑ የተከለሉ መንገዶችን ይዟል። ምዕራፍ አንድ ከተመረቀ በኋላ ወዲያውኑ የሁለተኛው ምዕራፍ (Friendship Park 2) የዲዛይንና የዝግጅት ሥራዎች ተጀምረዋል። በግንባታው ወቅት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም፣ ከሌላ ቦታ የተሰባሰቡ ከ4ሺህ በላይ አገር በቀል ትልልቅ ዛፎች (Indigenous trees) መጥተው በቦታው ላይ በተሳካ ሁኔታ እንዲተከሉ ተደርጓል። ግንባታው በጥቅምት 2015 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተመርቋል። 16 ሄክታር መሬት የሸፈነው ይህ ክፍል ከአብርሆት ቤተ-መጽሐፍት ፊት ለፊት የሚገኝ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ለሕፃናት፣ ለታዳጊዎችና ለቤተሰብ ስፖርታዊ መስተጋብር ተለይቶ የተገነባ ነው። በውስጡም እጅግ ዘመናዊና ሰፊ የሕፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን (Playgrounds)፣ ታዳጊዎች እየተጫወቱ ሳይንስና ቴክኖሎጂን የሚለማመዱበትን የሳይንስ ማዕከል፣ ትንንሽ የእግር ኳስ (Mini-football) እና የቅርጫት ኳስ (Basketball) ሜዳዎችን፣ የሩጫ ትራኮችን፣ ለወጣቶች ንባብ የሚሆኑ ቦታዎችን (Reading nooks) እና ከጎኑ ያለውን የሳይንስ ሙዚየም ግንባታን ያካተተ ሰፊ ይዘት አለው። የወዳጅነት ፓርክ ከብሔራዊ ቤተመንግሥት እስከ መስቀል አደባባይባለው አካባቢ የሚዘልቅ ዘመናዊ የሕዝብ መገልገያና መዝናኛ ማዕከል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፣ ይህ ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ ማስገኘት ችሏል። ይህም የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ራሳቸውን ችለው ከፍተኛ ገቢ ማመንጨት ከመቻል ባለፈ፣ በቱሪዝም ዘርፉ፣ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዘንድ ለበርካታ ዜጎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሰፊ የሥራ ዕድል እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እየፈጠረ ይገኛል። ከዚህ ኢኮኖሚያዊ እሴቱ ባሻገር፣ ፕሮጀክቱ የከተማ ነዋሪዎችን ማኅበራዊ ትስስር በከፍተኛ ደረጃ ያጠናክራል፤ የዜጎችን የኑሮ ጥራት፣ የጤና ሁናቴ እና ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ (Life style) ከማሻሻል አንጻርም የመደመር እሴት በተግባር መሬት ማወረዱንና የዜጎችን አገራዊ የባለቤትነት ስሜት በጽኑ የሚያሳድግ ትልቅ ማሳያ ነው። ፓርኩ ለጤና፣ ለአካል ብቃት፣ ለመዝናኛና ለንባብ ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ወጣቶች ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን በስፖርት፣ በዕውቀት ቀሰማና በሌሎች በጎ ነገሮች ላይ እንዲያሳልፉ ምቹ ከባቢ ፈጥሯል። በተጨማሪም ቦታው ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎችና ጎብኝዎች በየቀኑ በስፋት የሚገናኙበት ማዕከል መሆን ችሏል። በስፍራው ከቤተሰቦችና ሕፃናት፣ ከስፖርት ቡድኖችና ከሠርግ ተካፋዮች ጀምሮ እስከ ዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎች በከፍተኛ ቁጥር ይገኙበታል። ይህም ለሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች (Content Creators) ምቹ ከባቢ በመፍጠር፣ የአዲስ አበባን ዘመናዊና ማራኪ ገጽታ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ በስፋት እንዲያስተዋውቁና የከተማዋን በጎ ስም ለዓለም እንዲያደርሱ ትልቅ ዕድል ከፍቷል። ይህ ፓርክ አዲስ አበባን ለሌሎች የክልል ከተሞች በአረንጓዴ ልማት፣ በጽዳትና በዘመናዊ የሕዝብ መገልገያዎች በሞዴልነት የሚጠቀስ ሲሆን፣ የከተማዋን የዲፕሎማሲያዊ መዲናነት ገጽታ ይበልጥ በማደስ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች፣ ለዲፕሎማቶችና ለዓለም አቀፍ እንግዶች በጣም ሳቢና ተመራጭ መዳረሻ አድርጓታል። ፓርኩ በከተማዋ እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ውስጥ እየተገነቡ ላሉ ተመሳሳይ የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ቀዳሚ ማሳያ ሲሆን፣ እነዚህ አዳዲስ ቦታዎች እሴት የሚፈጥሩ፣ ዕድሎችን የሚያመቻቹ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያንን ባለቤትነት የሚያረጋግጡ ማዕከላት መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ያረጋግጣል።
የኮደሮች ኢኒሼቲቭ፡ የኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታና የወጣቶች ብሩህ መፃኢ ዕድል
Aug 10, 2026 112
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በዲጂታሉ ዓለም ያላትን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እና የወጣቶችን ክህሎት ለማልማት ያለመው የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ተጀምሯል። ይህ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች መካከል በተደረገ ትብብር የተዘጋጀ ሀገራዊ የዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ ፕሮጀክት ነው። ዋና ዓላማውም ወጣቶች በዲጂታሉ ዓለም ተወዳዳሪ እንዲሆኑና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈለጉ የቴክኖሎጂ ክህሎቶችን እንዲጨብጡ ማስቻል ነው። የስልጠናው መርሃ ግብር በኦንላይን ”Udacity” በተሰኘ ዓለም የትምህርት መድረክ በኩል የሚሰጥ ሲሆን፣ በዌብ ዲቨሎፕመንት፣ በዳታ አናሊቲክስ እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዋና ዋና ዘርፎች የተከፈለ ነው። ከእነዚህም ጎን ለጎን የንግድና ሥራ ፈጠራ እንዲሁም የመሪነት ክህሎት አጫጭር ስልጠናዎች ተካተዋል። እያንዳንዱ ኮርስ በግል ፍጥነት የሚወሰድ ሆኖ በአማካይ ከ6 እስከ 7 ሳምንታት የሚወስድ ሲሆን፣ ስልጠናውን በጥሩ ሁኔታ ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ሙሉ በሙሉ በነፃ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው የ’Udacity’ እና የኢኒሼቲቩ ይፋዊ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ይሰጣል። በዚህ ፕሮግራም ላይ ዕድሜው ከ13 ዓመት በላይ የሆነ ማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ የቀደመ የኮዲንግ እውቀት ሳይጠይቀው መመዝገብ ይችላል። ለመማር የሚያስፈልጉት ነገሮች የኢንተርኔት ግንኙነት ያለው ኮምፒውተር ወይም ስማርትፎን ብቻ ሲሆኑ፣ ምዝገባውም በይፋዊው 5millioncoders.gov.et ድህረ ገጽ በኩል ይከናወናል። የኢኒሼቲቩ የመጨረሻ ግቦች ሀገሪቱን በምስራቅ አፍሪካ እና በመላው አህጉር ውስጥ የቴክኖሎጂ ማዕከል ማድረግ እና የዲጂታል ስትራቴጂዎችን ማሳካት ናቸው። በተጨማሪም ሰልጣኞች በሀገር ውስጥና በውጭ ድርጅቶች እንዲቀጠሩ፣ ከቤት ሳይወጡ በዶላር የሚከፍሉ የርቀት ስራዎችን እንዲሰሩ እና የራሳቸውን የቴክኖሎጂ ስታርታፕ እንዲመሰርቱ መንገድ ይከፍታል። በቴክኖሎጂው ዘርፍ የሚታየውን የክህሎት እጥረት በመሙላትና ለሀገር የውጭ ምንዛሬ ገቢ በማስገኘት የወጣቶችን ተወዳዳሪነትና በራስ የመተማመን አቅም ያሳድጋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት ሀገራዊ ጥሪ፣ ይህ ክረምት በከንቱ እንዲያልፍ ሳይፈቀድ ወጣቶች በነጻ የሚሰጠውንና ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለውን ትምህርት እንዲወስዱ አሳስበዋል። አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ቀድመው የወሰኑ በመሆናቸው፣ ሌሎችም ይህንን እድል በመጠቀም የክረምቱ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት የተሳታፊዎችን ቁጥር ወደ ሰባት ሚሊዮን ለማድረስ የቀረበውን ጥሪ እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል። ይህንን ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስተናጋጅነት የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል። ዝግጅቱ የዘርፉን መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጭዎችን፣ የምስክር ወረቀት ያላቸውን የኢኒሼቲቩን ተመራቂዎች እና ወጣት ባለሙያዎችን በአንድነት ያገናኘ ሲሆን፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ ባተኮረ የኤግዚቢሽን ጉብኝት ተጀምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ሥዩም የመክፈቻ ንግግር ቀጥሏል። ኃላፊዋ የወጣቶች የቴክኒክና የዲጂታል ክህሎት ብቃት ወሳኝ ሀገራዊ ሀብት መሆኑን ገልጸው፣ የኮደሮችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የቀረበውን ጥሪ ተግባራዊነት አረጋግጠዋል። ቀጥሎ በተካሄደው የፓናል ውይይት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር አብዮት ባዩ፣ የጊሮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቤተልሔም ደሴ፣ እንዲሁም የኢኒሼቲቩ ምሩቃን የሆኑት አዝመራው ታደሰ እና የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ማኅሌት ሥዩም ልምዳቸውንና እይታቸውን አካፍለዋል። ፓናሊስቶቹ ወጣቶች ክህሎታቸውን ያለማቋረጥ እንዲያሳድጉ እና በኢትዮጵያ የዲጂታል ሥነ-ምህዳር ዕድገት ውስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ ያበረታቱ ሲሆን፣ መርሃ ግብሩም የኢኒሼቲቩን ከፍተኛ ሀገራዊ ሚና በድጋሚ ያረጋገጠ ሆኖ ማለፉን ጽህፈት ቤቱ አመልክቷል። የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ያላትን ራዕይ ለማሳካት የተጣለ ትልቅ መሰረት ነው። ወጣቶች በቴክኖሎጂው ዘርፍ የሚጨብጡት ዕውቀት የራሳቸውን የፈጠራ መንገድ ከመክፈቱም በላይ፣ ሀገሪቱ በምስራቅ አፍሪካና በአህጉሪቱ የቴክኖሎጂ ማዕከል ሆና እንድትወጣ ያስችላታል። በመሆኑም ይህን አጋጣሚ በአግባቡ መጠቀም ለሀገሪቱ ዘላቂ እድገትና ለወጣቱ ብሩህ ተስፋ ወሳኝ እርምጃ ነው።
የአፍሪካ የውሃ ማማ ኢትዮጵያ ሳትሆን ግብፅ ናት!
Aug 10, 2026 314
ግብጽ ራሷን የምትስልበት የውሃ እጥረት ትረካ ከነባራዊ ሁኔታም በእጅጉ የተቃረነ ነው። የአፍሪካን የታሪክ፣ የኢኮኖሚና ጂኦ-ፖለቲካ በከፍተኛ ሁኔታ ከሚቃኙት ተፈጥሯዊ ሃብቶች መካከል ውሃ ግንባር ቀደሙን ስፍራ ይይዛል። አፍሪካውያን የውሃ ሀብታቸውን በጋራ አልምቶ የመጠቀም ፍላጎታቸውና ጥረታቸው የአህጉሪቱን የወደፊት የልማትና የሰላም አቅጣጫ የሚወስን ወሳኝ ጉዳይ ቢሆንም ይህ አህጉራዊ የትብብርና የጋራ እድገት መንፈስ እውን ሊሆን የሚችለው የተፋሰሱ ሀገራት ያላቸውን እውነተኛ የውሃ ሀብት መጠንና ፍላጎት በሳይንሳዊ እውነታዎችና በግልጽኝነት ላይ ተመስረተው ሲተገብሩት ብቻ ነው። በዚህ አህጉራዊ የተፋሰስ ትብብር ውስጥ ትልቁን ስፍራ የሚይዘው የታላቁ ዓባይ ወንዝ ተፋሰስ ነው። ሆኖም ለዘመናት የዘለቀውና አሁንም ድረስ በዲፕሎማሲው መድረክ የሚንጸባረቀው ዋነኛው ማነቆ ግብፅ እራሷን "ለከፍተኛ የውሃ እጥረት የተጋለጠችና ፍጹም የዓባይ ጥገኛ የሆነች ብቸኛ ሀገር" አድርጋ የምታቀርብበት ትርክት ነው። ይህ ትረካ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብን ሲያደናግር ቆይቷል። ነገር ግን የጂኦግራፊ፣ የሃይድሮሎጂና የዘመናዊ ቴክኖሎጂ መረጃዎችን በጥልቀት ስንመረምር ግብፅ እራሷን የምትስልበት የውሃ እጥረት ትረካ ከእውነተኛው ነባራዊ ሁኔታ ጋር በእጅጉ የሚቃረን ሆኖ እንገኘዋለን። ግብፅ በውስጧ የያዘቻቸውን ግዙፍና ያልተነኩ ድብቅ ሀብቶች፣ የቴክኖሎጂ አቅሞችን እና በበረሃ ውስጥ የምታከናውናቸውን ሰፋፊ የውሃ ማዞር ፕሮጀክቶች ስንመለከት ሀገሪቱ እውነተኛ የውሃ እጥረት ሳይሆን ከፍተኛ የውሃ ሀብት ያላት መሆኗን በግልጽ ያሳያል። ይህንን እውነታ በግልጽ የሚያስረዱትንና የግብፅን እውነተኛ የውሃ ማማነት የሚያረጋግጡትን ዋና ዋና ሳይንሳዊና ተግባራዊ ማስረጃዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦ የከርሰ ምድር ውሃ ከገፀ-ምድር ውሃ ባሻገር በግብፅ፣ ሊቢያ፣ ሱዳን እና ቻድ ስር የሚገኘው የኑቢያ አሸዋማ ድንጋይ የከርሰ-ምድር ውሃ ስርዓት (Nubian Sandstone Aquifer System) በዓለም ላይ ካሉ የከርሰ-ምድር ውሃዎች ትልቁ ነው። አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት በግብፅ ግዛት ስር ብቻ የሚገኘው የዚህ ውሃ መጠን ከ5 ትሪሊዮን እስከ 10 ትሪሊዮን ኪዩቢክ ሜትር እንደሆነ ይገመታል። ይህ ግዙፍ ሀብት የዓባይ ወንዝን የአምስት ክፍለ-ዘመናት (500 ዓመታት) አጠቃላይ የውሃ ፍሰት የሚበልጥ ድብቅ ሃብት ነው። ግብፅ ይህንን ሀብቷን በዘመናዊ መንገድ አውጥታ ብትጠቀም ለበርካታ አስርት ዓመታት ያለ ምንም የገፀ-ምድር ውሃ ስጋት መኖር የሚያስችላት ስትራቴጂካዊ ክማቸት አላት ማለት ነው። የአስዋን ከፍተኛ ግድብና የናስር ኃይቅ የግብፅ የውሃ መከላከያ ማዕከል የሆነውና በአስዋን ከፍተኛ ግድብ የተገደበው ናስር ሀይቅ እስከ 169 ቢሊዮን ኩቢክ ሜትር ውሃ የመያዝ አቅም አለው። ይህም ማለት በናስር ሃይቅ የተከማቸው ውሃ ብቻ የግብፅን የዓመታት ሙሉ የውሃ ፍላጎት ያለ ምንም ተጨማሪ የወንዝ ፍሰት መሸፈን የሚያስችል ግዙፍ ስትራቴጂካዊ መያዣ (Buffer) ሆኖ ያገለግላል። የባሕር ውሃ ማጣራት አቅምና የግብጽ 2050 ማስተር ፕላን ግብፅ በሜዲትራኒያን እና በቀይ ባህር ረጅም የባህር ዳርቻዎች ያሏት በመሆኑ በጨዋማ ውሃ ማጣሪያ ቴክኖሎጂ ትልቅ እርምጃ እየወሰደች ትገኛለች። በአሁኑ ወቅት በቀን ከ1 ነጥብ 5 እስከ 2 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተጣራ ውሃ እያመረተች ሲሆን፤ በግልና በሕዝብ ፣ በካርቦን ቅነሳ ድጋፎች እና በባህር ዳርቻ ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች አማካኝነት የማጣራት አቅሟን በጥሬው በእጥፍ ለማሳደግ የሚያስችል እስከ 2050 የሚዘልቅ ስትራቴጂካዊ ማስተርፕላን አዘጋጅታለች። ግዙፍ የውሃ ማዞር ፕሮጀክቶች ግብጽ በቶሽካ ፕሮጀክት አማካኝነት ከናስር ሀይቅ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ኩቢክ ሜትር ውሃዎችን ወደ ምዕራብ በረሃ በመቀየር ሰው ሰራሽ ሀይቆች እና ክፍት የመስኖ ቦዮች እንዲፈጠሩ አድርጋለች ። በሌላ በኩል በኒው ዴልታ እና ጂሪያን በሚሊዮን ሄክታር መሬት ለማልማት እና አዳዲስ ከተሞችን ለመገንባት የተፈጥሮ የአባይ ወንዝን አቅጣጫ በመቀየር ቢሊዮን ኩቢክ ሜትር ውሃ በመመደብ ላይ ትገኛለች።እነዚህ ፕሮጀክቶች ግብፅ ለትልልቅ የበረሃ ልማቶች የሚተርፍ ትርፍ ውሃ እንዳላት በተግባር የሚያሳዩ ናቸው። ውሃን መልሶ የመጠቀም አቅም ግብፅ ውሃን መልሶ በማጣራት ጥቅም ላይ ለማዋል ትልልቅ የውሃ ማጣሪያ ጣቢያዎችን ለምሳሌ በህር ኤል ባቃር (Bahr El-Baqar plant) ገንብታለች። ሀገሪቱ በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ኩቢክ ሜትር ፍሳሽ ውሃዎችን መልሳ በመጠቀም ለግብርና በማዋል የምትጠቀመውን እያንዳንዱን የውሃ ጠብታ የማባዛት ከፍተኛ ቴክኖሎጂያዊ አቅም እንዳላት አስመስክራለች። መደምደሚያ አፍሪካውያን የውሃ ሀብታቸውን በጋራ አልምተው ለመጠቀም የሚያደርጉት ጉዞ እውን ሊሆን የሚችለው ግብጽ የምታራምደውን አይነት የተሳሳቱ ትርክቶችን በሳይንሳዊ እውነታዎች መተካት ሲቻል ብቻ ነው። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ይህን በሚገባ ሊገነዘብ ይገባል። ግብፅ ግዙፍ የከርሰ-ምድር ውሃ፣ ዘመናዊ የውሃ ማጣሪያ ጣቢያዎች፣ ከፍተኛ የውሃ መልሶ መጠቀም አቅም እና በበረሃ ውስጥ ውሃ እስከ ማዞር የሚያስችል ሀብት ያላት ሀገር ናት። ይህም ግብፅ የውሃ እጥረት ያለባት ሀገር ሳትሆን፣ የአፍሪካ የውሃ ማማ መሆኗን በተግባር የሚያሳይ ነው።
ኢትዮጵያ፤ አዲሲቷ የዘመን ተሻጋሪ ዲጂታል ክህሎት የተስፋ አድማስ
Aug 7, 2026 244
በሀሪ መልስ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በወፍ በረር “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ ተጠናቋል። በዛሬው ዕለትም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ አስጀምረናል። ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር፣ እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሠረታዊ ትልሞች ናቸው። እነዚህ ትልሞች እንዲሳኩም በተለይ የሕዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማትን ማስፋት ላይ ትልቅ ሥራ የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ሥራዎች የመደመር መንግሥት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ ናቸው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ዲጅታላይዜሽን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የሚመራ ብሔራዊ የልማትና ዕድገት ፕሮግራም ነው። እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2020 በዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ማዕቀፍ ይፋ የተደረገው ብሔራዊ አጀንዳ በዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂም ቁልፍ ጉዳይ ሆኖ ተይዟል። ግቡም ሁሉንም ተቋማት በኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ በማስተሳሰር በኢትዮጵያ ፈጣን የዲጅታል ኢኮኖሚ ሽግግር መፍጠር ነው። ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት፣ የኢንተርኔትና የዲጅታል ትስስርን ማስፋፋት፣ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎትን ማላቅ፣ ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ የጤና አጠባበቅና የትምህርት ሥርዓትን ማሻሻል፣ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የዲጅታል ኢኮኖሚ መገንባት፣ በኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ እንዲሁም በኢኖቬሽን የሥራ ዕድል መፍጠር እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማትን መደገፍ የዲጅታላይዜሽን መሠረቶች ናቸው። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የዲጅታል ኢኮኖሚ መሠረት ጥሏል። በመንግሥት ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥን በዲጅታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል፤ ተጠያቂነት የሰፈነበት የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋትም ብልሹ አሠራርን ለመከላከል የሚያስችል መሠረት ጥሏል። የዲጅታል ማንነትን በማስፋፋት ዜጎች አገልግሎቶችን በኤሌክትሮኒክ ሥርዓት ማግኘት እንዲችሉ ያስቻለ ሲሆን፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን፣ ቅንጅትንና ተደራሽነትንም አሳድጓል። ቀደም ሲል ዜጎች ዲጅታል ማንነት መጠቀም በማይችሉበት ወቅት በርካታ የወረቀት ሰነዶችን ከማቅረብ ጀምሮ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትን በመዳረስ ረጅም ጊዜና ጉልበት ያጠፉ ነበር። አሁን ግን ሁኔታው ተለውጧል። በወረቀት አልባ ሥርዓት ፈጣንና ፍትሐዊ የመንግሥት አገልግሎት ማግኘት የሚቻልበት የዲጅታል ምህዳር ተፈጥሯል፤ የዜጎች እንግልት ቀንሷል፤ ወረፋና ጥበቃም ተረት ሆኗል። የዲጅታል ክፍያ ሥርዓትም በኢትዮጵያውያን ዘንድ እንደዕለት ተዕለት አጠቃቀም ቀላልና የተለመደ እየሆነ መጥቷል። የቴሌኮም መሠረተ ልማትን የማስፋፋት ሥራም ተጠናክሯል፤ የዲጅታል ክህሎት በተለይም በወጣቶች ዘንድ አዲስ የእውቀትና የተወዳዳሪነት መሣሪያ ሆኗል። ለዲጅታል መሠረተ ልማት መስፋፋት ቁልፍ የሆኑ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፎችም ተፈጥረዋል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ለኢትዮጵያ የዲጅታል ኢኮኖሚ ሽግግር መሠረት ጥሏል፤ የኢትዮጵያን መጪ ጊዜ በተስፋ መመልከት የሚያስችል አጉሊ መነጽር አቅርቧል። በዲጅታል ክፍያዎች የታገዘ የጥሬ ገንዘብ አልባ ግብይትም የሀገሪቱን አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እያዘመነ ይገኛል። ጥሬ ገንዘብ በእጅ የመያዝ ልማድ መቀነሱ የገንዘብ ማተሚያና ማጓጓዣ ወጪን ቀንሷል፤ የገንዘብ ዝውውርን ግልጽና ፈጣን በማድረግም ሕገወጥ አሠራሮችንና ሙስናን ለመከላከል አስችሏል። ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ጥበቃ ከተደረገለት የፋይናንስ ሥርዓት ጋር ሲቀናጅም፣ ሕዝቡ በዲጅታል ክፍያዎች ላይ ያለው መተማመን እንዲጎለብት ያደርጋል፤ የሀገሪቱንም የዲጅታል ሽግግር ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል። ይህም ለዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሠረት ጥሏል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030፤ የሽግግሩ ቀጣይ ምዕራፍ የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የመንግሥትና የግል ዘርፍ አጋርነትን በማጠናከር፣ የኤሌክትሮኒክ የመንግሥት አገልግሎቶችን ፍጥነት፣ ተደራሽነትና ግልጽነት ለማሳደግ ያለመ ነው። ይህም የመንግሥትን ወጪ ለመቀነስና የአገልግሎት ብቃትን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬትም በኢኮኖሚ፣ በትምህርትና በአገልግሎት ዘርፎች አዎንታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። የሀገሪቱ የዲጅታል ሽግግር በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ላይ በተመሠረተው የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ላይ የተቃኘ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስትራቴጂ ማስጀመሪያው ወቅት፦ ስትራቴጂው በከተማም ሆነ በገጠር የዲጅታል ሥርዓትን በማስረጽ የዲጅታል ኢኮኖሚን እውን የምናደርግበት ነው ብለዋል። ቁሳዊ ዕድገት የሚጀምረው የሰው ኃይል አቅምን በመገንባት እንደሆነ ጠቅሰው፣ ወጣቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ፣ የፈጠራ ባለቤቶችና ሥራ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ በዲጅታል ክህሎት ማስታጠቅ እንደሚገባ አጽንዖት ሰጥተዋል። የዲጅታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂያዊ ግቦች ኢትዮጵያ የብሮድባንድና ኢንተርኔት ተደራሽነትን በመላ ሀገሪቱ በመዘርጋት፣ የዜጎችና ተቋማትን የዲጅታል ክህሎት በማሳደግ፣ እንደ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ስታርትአፖችን በቴክኖሎጂ በማዘመን የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትና ንግድን መሳብ፣ እንዲሁም አካታች የዲጅታል ኢኮኖሚ መገንባት ናቸው። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የመንግሥት የዲጅታል አገልግሎት ማስፋፊያ፣ የቴሌኮም ሪፎርም፣ ዲጅታል ክፍያ፣ ብሔራዊ የዲጅታል መታወቂያ/ፋይዳ፣ እንዲሁም በሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ ዲጅታል የሕዝብ መሠረተ ልማት፣ የሳይበር ደህንነትና ብሔራዊ የዲጅታል አካታችነትን መርህ ያደረገውን የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አዋልዷል። የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጅታል ሽግግር ስትራቴጂ ነው። ከዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬት የተቀዳ ታላቅ የመሆን ህልም ሥጋ ለብሶ የታየበት ግልጽ ፍኖተ ካርታም ነው። የዲጅታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም፣ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2030 ቀልጣፋ የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ፣ የአስተዳደር ሥርዓትን በማጠናከር አገልግሎትን ማሻሻል፣ በዲጅታል ቴክኖሎጂ የበቃ ማኅበረሰብ በመፍጠር ሀገርን ማበልጸግ፣ ለነገ ዛሬ የሚኖር አደራና ዛሬ የነገ ስንቅ ሆኖ በግልጽ ሰፍሯል። የኢትዮጵያ የዲጅታል ሽግግር ግብ አንድ ነው፤ አካታችና ዘላቂ ዲጅታል ኢኮኖሚ መገንባት፣ በዋጋ ተመጣጣኝና ተደራሽ የኢንተርኔትና የኮሙኒኬሽን አገልግሎትን ማስፋት፣ በዲጅታል ኢኮኖሚ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የመረጃ አስተዳደርና የሳይበር ደህንነት ጥበቃን ሕልው ማድረግ፣ የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትን መጨመር፣ ዲጅታል ክህሎትና ኢኖቬሽንን ማሳለጥ ነው።   ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ /ፋይዳ/፤ የዲጅታል ሽግግር መልህቅ ''በቅርብ ዓመታት ውስጥ፣ ዲጅታል ማንነት ተስፋ ሰጪ ከሆነው ፈጠራ ወደ ዲጅታል ሽግግር መሠረታዊ ምሰሶ ተሻሽሏል። ከአሁን በኋላ አማራጭ ሳይሆን፣ ሰዎችን ከአገልግሎቶች፣ ከማኅበረሰቦች፣ ከተቋማት እና ከመንግሥታት ጋር የሚያገናኝ አስፈላጊ መሠረተ ልማት ነው። ፋይዳ ካርድ ብቻ አይደለም። የግለሰቦችን የግል መረጃ ምሥጢራዊነት በመጠበቅና አስፈላጊ የሆነውን መረጃ ብቻ በማጋራት ማንነትን የሚያረጋግጥ ልዩ መለያ ቁጥር ነው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ /ፋይዳ/፤ የዲጅታል ሽግግር መልህቅ የዲጅታል ብሔራዊ መታወቂያ /ፋይዳ/ (National Digital ID) በኢትዮጵያ ሥራ የጀመረው እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2023 ነበር። ምንም እንኳን የፕሮጀክቱ ዝግጅትና ሕጋዊ መሠረት ቀደም ብሎ የተጀመረ ቢሆንም፣ በአዋጅ ቁጥር 1284/2015 በሕግ ተቋቁሟል። እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር ከ2019 እስከ 2020 ባለው ጊዜም ፋይዳ በዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ አካል ሆነ። ከዚያም ምዝገባው በመላ ኢትዮጵያ ተስፋፍቶ፣ ከመንግሥት አገልግሎቶች፣ ከባንኮች፣ ከዲጅታል ክፍያ ሥርዓት እና ከመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት ጋር ተሳስሯል። በኢትዮጵያ እያንዳንዱን ነዋሪ የአንድ ልዩ የዲጅታል መለያ ባለቤት ማድረግ የፕሮጀክቱ ዋነኛ ግብ ነው። ይህም የመንግሥትና የግል አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘት የሚቻልበትን ሥርዓት ለመዘርጋት፣ የማንነት ማጭበርበርና ድርብ ምዝገባን ለማስቀረት እንዲሁም የኢትዮጵያን ዲጅታል ኢኮኖሚ ለመደገፍ ያስችላል። ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የነዋሪዎችን የባዮሜትሪክና ዲሞግራፊክ መረጃ በመሰብሰብ፣ ''አንድ ሰው፣ አንድ ማንነት” በሚል መርህ እያንዳንዱን ሰው ልዩ በሆነ ሁኔታ መለየት የሚያስችል ሥርዓት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ስለፋይዳ አስፈላጊነት ሲናገሩ፣ “ፋይዳ በአማርኛ፣ በኦሮሚኛ፣ በትግርኛ፣ በሱማሊኛ፣ በአፋርኛ እንዲሁም በአረብኛ፣ በሂንዱኛና በተርኪሽ ቋንቋዎች ፋይዳ ነው። … ዲጅታል መታወቂያ /ፋይዳ/ በጣም ጠቃሚ ነገር ነው፤ ከሕዳሴ የሚያንስ አይደለም። እንደ ሀገር ዲጅታል መታወቂያ ብንሠራ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርት በሰባት ፐርሰንት ይጨምራል። ፋይዳ የመተማመኛ ሥርዓት ነው…” በማለት የፋይዳን መልከ ብዙ ፋይዳ ገልጸዋል። ፋይዳ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና የዲጅታል ኢኮኖሚ ሽግግሩን ለማሳለጥ ቁልፍ መሣሪያ መሆኑንም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ከ150 በላይ ተቋማት ጋር ተሳስሯል። ከ48 ሚሊዮን በላይ ዜጎችም ተመዝግበዋል። እስከ 2020 ዓ.ም ድረስ የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ወደ 115 ሚሊዮን ለማድረስ ጉዞው ቀጥሏል። በዚህም በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ወደ መደበኛ የፋይናንስ ሥርዓት ለማስገባት እያገዘ ይገኛል። መንገዶች ሁሉ ኢትዮጵያን ወደ ዲጅታል ሽግግር በሚወስዱበት ሀዲድ፣ ፋይዳ መሪ ተዋናይ ሆኖ ይቀጥላል። ዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት እንዲያገኙ፣ የባንክና የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲጠቀሙ የሚያስችል የቴክኖሎጂ ምህዳር ይፈጥራል። መንግሥትም ማጭበርበርን ለመከላከል፣ በተቋማት መካከል ግልጽና የተቀናጀ ትብብርን ለመዘርጋት እና የተሻለ የሕዝብ አገልግሎት የሚሰጥበትን ዕድል እውን ለማድረግ ፋይዳን ይጠቀማል። የቢዝነስ አንቀሳቃሾችም ዲጅታል ግብይትን፣ ፋይናንስንና ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሥራቸውን የበለጠ ቀልጣፋና ተደራሽ ማድረግ ይችላሉ። በአጭሩ፣ ፋይዳ ''ሁሉ በእጄ፣ ሁሉ በደጄ” የሚለውን የዲጅታል ኢኮኖሚ ራዕይ እውን ለማድረግ የሚያግዝ ቁልፍ መሠረተ ልማት ነው።   መሶብ፤ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት የጊዜና የቦታ ልጓም ''ሀገራዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሠረታዊ የሆነ የባህል ለውጥ ያስፈልጋል። ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን እንገኛለን። መሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትን ተግባራዊ ማድረግ የጀመርነው በቅርብ ጊዜ ቢሆንም፣ በመሶብ አገልግሎቶች የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የዚህን የሥራ ሞዴል ውጤታማነት በግልጽ አረጋግጧል። ይህም አሠራሩን ይበልጥ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ያመላክታል።”ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት፤ የጊዜና የቦታ ልጓም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 12 የፌዴራል ተቋማት 40 የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር እንዲሰጡ በማድረግ ሚያዚያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቆ ሥራ ጀምሯል። እነሆ ማዕከሉ የተቋማትንና የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ቁጥር እያሳደገ የኢትዮጵያን የዲጅታል ሽግግር ፍኖት እየቀረጸ ይገኛል። ዜጎችም በዲጅታል መሠረተ ልማት የተደገፈ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል። ከዚህ በፊት የዜጎችን ጊዜ የሚያባክኑ ረጅም ወረፋዎች፣ የተለያዩ ቢሮዎችን ደጋግሞ መጎብኘት፣ “ሰነድ ይጎድላል፣ ኮፒ አድርገህ አምጣ” የሚሉ የወረቀት ሥራዎች በአዲሱ የአገልግሎት ሥርዓት እየተቀየሩ ነው። አዲስ የአገልግሎት አድማስ የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ220 በላይ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ሕንፃ ሥር በማቅረብ የዜጎችን የጊዜና የቦታ ጫና ቀንሷል። ከቀበሌ መታወቂያ ማውጣት ጀምሮ እስከ ከፍተኛ የንግድና የጉምሩክ አገልግሎቶች ድረስ በቀላሉ ማግኘት የሚቻልበት ምቹ ምህዳር ተፈጥሯል። ፈጣንነት፣ ቅልጥፍና፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና መርሆዎች ሆነዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ባስጀመሩበት ወቅት፤ ዜጎቻችን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ትርጉም ያለው የጊዜ ቁጠባ እንዲያገኙ ለማስቻል፣ እነዚህን የተቀናጁ አገልግሎቶች ይበልጥ ተደራሽ የማድረግ ሥራችንን እንቀጥላለን ብለዋል። የዲጅታል አገልግሎት የዜጎችን ጊዜና ጉልበት የሚቆጥብ አዲስ የአስተዳደር ባህል መሆኑን ገልጸዋል። በአጠቃላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የወረቀት እና የወረፋ ዘመንን በመቀየር ዜጋን ማዕከል ያደረገ፣ ቀልጣፋና ዲጅታል የሆነ የአገልግሎት ሥርዓት እየገነባ ያለ የለውጥ ምሳሌ ሆኗል።     የ5-ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ፤ የዲጅታል ክህሎት ማበልጸጊያ መድረክ በዲጅታል ዘመን የሰው ኃይል አቅም የሀገራት የዕድገት መሰረት እሆነ ነው። ኢትዮጵያም የወጣቶቿን የፈጠራና የቴክኖሎጂ አቅም ለማሳደግ ትልቅ የዲጅታል ክህሎት ማበልጸጊያ መርሃ ግብር ጀምራለች። የ5-ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢንሼቲቭ የወጣቱን ትውልድ የፕሮግራሚንግ፣ የሶፍትዌር ልማት፣ የፈጠራ ሥራና የዲጅታል ቴክኖሎጂ አቅም ለማጎልበት የተቀረፀ ሀገራዊ አጀንዳ ነው። መርሃ ግብሩ ወጣቶችን የዲጅታል ኢኮኖሚ ተሳታፊዎች ብቻ ሳይሆኑ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎችና የሀገር በቀል መፍትሔ አበልጻጊዎች ለማድረግ ያለመ ነው። ''ይህም ኢትዮጵያ በዓለም የዲጅታል ውድድር ውስጥ የምትኖራትን ሚና ለማሳደግ፣ የቴክኖሎጂ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና በአፍሪካ የፈጠራ ማዕከል ለመሆን የሚያግዝ የወደፊት ራዕይ ነው። ኢትዮጵያ ወደፊት የሚያልሙ አሳቢ ወጣት ዜጎቿ ተስፋ አላት። የ‘አምስት ሚሊዮን ኮደርስ’ መርሃ ግብር ታላቅ እድል ነው። አምስት ሚሊዮኖቹ ኮደሮች ሀገር በቀል መፍትሔዎችን የሚሰጡ ብቻ ሳይሆኑ፣ ለአህጉራችን የተስፋ ብርሃን የሚፈነጥቁ ናቸው።''ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአጠቃላይ 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ የዲጅታል ክህሎትን ከመገንባት ባሻገር፣ የወጣቱን የፈጠራ ኃይል ወደ ሀገራዊ የዕድገት ሞተር ለመቀየር የተቀረፀ የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ዋነኛ መሠረት ነው። 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢንሼቲቭ፤ የዲጅታል ክህሎት ማበልጸጊያና የወጣቱ የወደፊት አቅም በፍጥነት በሚለዋወጠው የዲጅታል ዓለም ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት መያዝ አማራጭ ሳይሆን የዘመኑ ግዴታ ሆኗል። ዛሬ ላይ በመትጋት ነገን ማልማት የእያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት ሲሆን፣ የሀገር ዕድገትም የሰው ኃይል አቅም ግንባታ ላይ ይመሰረታል። መንግሥት የበለጸገችና በቴክኖሎጂ የተደገፈች ኢትዮጵያን ለመገንባት ከለያቸው አምስት ቁልፍ የትኩረት መስኮች መካከል አይ.ሲ.ቲ (ICT) አንዱ ነው። በዚህ ራዕይ መሠረት የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማሳለጥ ሦስት ቁልፍ የዲጅታል ሽግግር ማስፈጸሚያዎች ተግባራዊ ሆነዋል። እነሱም መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት፣ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ (ፋይዳ) እና 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ ናቸው። የወጣቱን የዲጅታል አቅም የሚገነባ ታላቅ ኢንሼቲቭ 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ በኢትዮጵያና በተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ትብብር ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ በሦስት ዓመታት ውስጥ 5 ሚሊዮን ወጣቶችን በዲጅታል ክህሎት ለማሰልጠን የተቀረጸ ፕሮግራም ነው። ፕሮግራሚንግ (Programming)፣ የመረጃ ትንተና (Data Analysis)፣ የአንድሮይድ ልማት (Android Development) እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት መሠረቶች (Artificial Intelligence Fundamentals) የሥልጠናው ዋና የክህሎት ዘርፎች ናቸው። ኢንሼቲቩ የተያዘለትን ግብ በፍጥነት እያሳካ ይገኛል። ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ከ5 ሚሊዮን በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበዋል፤ ቁጥሩን እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም 7 ሚሊዮን ለማድረስ ዕቅድ ተይዟል። ይህም የወጣቶችን ለሥራ ዓለም ተፈላጊነት ከማሳደግ ባሻገር፣ የሀገሪቱን የዲጅታል የሰው ኃይል ልማት ያጠናክራል። በመንግሥት ተቋማት የሶፍትዌር ልማትና የዲጅታል ሽግግር ሥራዎችን የሚያሳልጡ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችንም ያፈራል። በኢንሼቲቩ አማካኝነት 1 ሚሊዮን የዲጅታል የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ከዲጅታል ምርቶች ወጪ ንግድ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት የተቀመጠው ዕቅድ የፕሮግራሙን ሀገራዊ ፋይዳ ያመላክታል። የወጣቶች የፈጠራ ኃይል የኢትዮጵያ የዲጅታል ተስፋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየትኛውም የትምህርትና የዕውቀት ደረጃ ላይ ያሉ ወጣቶች የአምስት ሚሊዮን ኮደሮች ፕሮጀክትን በመጠቀም ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ ጥሪ አቅርበዋል። የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከላት፣ አሰልጣኞችና ዩኒቨርሲቲዎችም የፕሮግራሙን ስኬት ለማስፋት የሚያደርጉት አስተዋፅኦ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጅታል ሽግግር ሦስቱ ምሰሶዎች በጥቅሉ 5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ፣ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ (ፋይዳ) እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የኢትዮጵያን የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያስፈጽሙ ተያያዥ ምሰሶዎች ናቸው። ኮደርስ የዲጅታል ኢኮኖሚውን የሚገነባና የሚያስፋፋ የሰው ኃይል ያበረክታሉ፤ ፋይዳ ደግሞ የደህንነቱ የተጠበቀ የዲጅታል ማንነት ሥርዓት ይፈጥራል፤ መሶብም በአንድ ጣሪያ ሥር ፈጣንና ግልጽ የህዝብ አገልግሎት ያሳልጣል። ከዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ራዕይ ጋር ተጣምረው እነዚህ ሦስት የለውጥ ምሰሶዎች ኢትዮጵያን ወደ አካታች፣ ዘላቂና ተወዳዳሪ የዲጅታል ኢኮኖሚ ለማሸጋገር የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው።   ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የኢትዮጵያ ተሻጋሪ ህልሞች መመልከቻ በኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እ.ኤ.አ. በ2020 የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በመመስረት ተቋማዊ መሠረት የያዘ የልማት አቅጣጫ ሆኗል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፖሊሲና ሕጋዊ ማዕቀፎች በመዘርጋታቸው ዘርፉ በተደራጀ አሠራር እንዲመራ ተደርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጎበኙበት ወቅት፣ ሰው የጠራ ራዕይ ካለው፣ በከፍተኛ ዲሲፕሊን የሚሠራ ከሆነ ያሰበውን ማሳካት እንደሚችል፤ ኢትዮጵያ ብቃት ያላት ሀገር መሆኗን በመግለጽ የዘርፉን ሀገራዊ ጠቀሜታ አስረድተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሀገር ውስጥ የፈጠራ አቅምን በማበረታታት ዘርፈ ብዙ ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች እንዲመነጩ እያደረገ ይገኛል። በግብርና፣ በጤና፣ በፋይናንስ፣ በደህንነትና በአገልግሎት ዘርፎች የሚያገለግሉ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መፍትሔዎች በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች መፍጠር ጀምረዋል። በአማርኛ፣ ኦሮምኛና ትግርኛ ቋንቋዎች የተዘጋጁ የጽሑፍና የድምፅ ማቀናበሪያ ቴክኖሎጂዎች (NLP)፣ በጤና ዘርፍ የጡት ካንሰር፣ የስኳር በሽታና የሳንባ በሽታዎችን በምስል ምርመራ ቀድመው ለመለየት የሚያግዙ የAI መፍትሔዎች፣ በግብርና ዘርፍ የቡናና የሰብል በሽታዎችን የሚለዩ መተግበሪያዎች እየተስፋፉ ነው። በተጨማሪም ለከተማ ደህንነት፣ ለፖሊስ ሥራ፣ ለጉምሩክ ቁጥጥርና ለፋይናንስ ተቋማት የሚያገለግሉ ቻትቦቶችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች በመስኩ እየተተገበሩ ይገኛሉ። የታዳጊዎች የሰመር ካምፕ የAI ስልጠናዎችም የወደፊቱን የቴክኖሎጂ ባለሙያ ትውልድ ለማፍራት እያገዙ ናቸው። የኢትዮጵያ የዲጅታል ሽግግርና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ጉዞ በሀገር ድንበር የማይገደብ፣ የአፍሪካን ዲጂታል ሽግግር ታሳቢ ያደረገ አህጉራዊ ራዕይ ነው። ለዚህም ኢትዮጵያ የፓን አፍሪካ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኮንፈረንስን በማዘጋጀት አፍሪካ በዲጂታል ሽግግር፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ ትብብር እንድትጠናከር ያላትን ራዕይ አሳይታለች። በአፍሪካ ቀዳሚ ከሚሆኑ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከላት አንዱ የሆነው የAI ዩኒቨርሲቲ ግንባታም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ለማሳካት፣ የአፍሪካን የቴክኖሎጂና የፈጠራ አቅም ለማሳደግ የተያዘ ተሻጋሪ ራዕይ ነው። በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ለኢትዮጵያ የወደፊት የዕውቀት ኢኮኖሚ፣ የፈጠራ አቅምና የዲጂታል ሉዓላዊነት መሠረት እየሆነ የሚሄድ ተሻጋሪ መሣሪያ ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር፤ የዲጅታል ሉዓላዊነት እና ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ዘብ የዓለም የዲጅታላይዜሽን ሽግግር በብርሃን ፍጥነት እየተስፋፋ ባለበት ዘመን፣ ቴክኖሎጂን መጠቀም ብቻ ሳይሆን የዲጅታል መሠረተ ልማቶችን ከሳይበር ስጋቶች መጠበቅ የሀገራት ቁልፍ ተግባር ሆኗል። በዚህ የቴክኖሎጂ ውድድር ዓለም የመረጃ ደህንነት ከቴክኒክ ጉዳይ ባለፈ የሀገር ሉዓላዊነትና ህልውና ጉዳይ እየሆነ መጥቷል። ኢትዮጵያም የዘግይቶ መግባት ጥቅም (Latecomer Advantage) በመጠቀም የዲጅታል ሽግግሯን በዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ላይ ለመገንባት እየሠራች ትገኛለች። ይህንን የዲጅታል ጉዞ አስተማማኝ ለማድረግና የሀገሪቱን የመረጃ ሀብት ለመጠበቅ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ወሳኝ ሚና እየተወጣ ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የኢትዮጵያን የኢንፎርሜሽን ሥርዓቶችና ቁልፍ የመረጃ መሠረተ ልማቶች ከሳይበር ጥቃት የመጠበቅ፣ የመረጃ ደህንነትን የማረጋገጥና ብሔራዊ ጥቅሞችን የማስከበር ተልዕኮ ተሰጥቶታል። የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ፣ የደህንነት ኦፕሬሽን ማዕከላት (Security Operation Centers) እና የዲጅታል ፎረንሲክ ላቦራቶሪዎች ግንባታ ለዘርፉ የተሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። እነዚህ ዘመናዊ የዲጅታል ደህንነት መሠረተ ልማቶች እንደ ባንክ፣ ቴሌኮም፣ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ቁልፍ ሀገራዊ ተቋማትን ከተወሳሰቡ የሳይበር ጥቃቶች አስቀድሞ ለመከላከል፣ አደጋ ቢከሰትም ፈጣን ሕጋዊና ቴክኒካዊ ምላሽ ለመስጠት ያስችላሉ። የመረጃ ደህንነት፤ የዲጅታል ኢኮኖሚ መሠረት በዛሬው ዓለም መረጃ (Data) እንደ አንዱ ዋና ሀብት በመቆጠሩ፣ የዜጎችን ግላዊ መረጃ፣ የፋይናንስ ግብይቶችንና የመንግሥት ሚስጥራዊ መረጃዎችን በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ የዲጅታል ሉዓላዊነት ዋና መሠረት ሆኗል። ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ሥርዓት መኖሩ ዜጎች በዲጅታል አገልግሎቶች ላይ እምነት እንዲያሳድሩ፣ የግልና የውጭ ባለሀብቶችም በኢትዮጵያ የዲጅታል ኢኮኖሚ ላይ የተሻለ እምነት እንዲኖራቸው ያደርጋል። በዚህም የሳይበር ደህንነት የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ስኬትን የሚደግፍ ዋና የጥበቃ መሠረት ሆኖ ይቀጥላል። ማጠቃለያ፡ ዲጂታል ኢትዮጵያ፤ የወደፊት ተወዳዳሪነት መሠረት የኢትዮጵያ የዲጂታል ሽግግር ጉዞ ከፖሊሲ ቀረጻ እስከ ተግባራዊ የዲጂታል መሠረተ ልማት ዝርጋታ በፍጥነት እየተሻገረ ይገኛል። ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሚመራ ሲሆን፣ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ /ፋይዳ፣ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት፣ አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ልማትና የሳይበር ደህንነት ሥርዓት ዋና ዋና የሽግግሩ ምሰሶዎች ሆነዋል። ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ /ፋይዳ የዜጎችን ዲጂታል ማንነት በማረጋገጥ ለዲጂታል አገልግሎቶች መሠረት ሲሆን፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሕዝብ አገልግሎትን በፍጥነት፣ በቅልጥፍናና በግልጽነት ለማቅረብ አዲስ የአሠራር ባህል እየገነባ ነው። አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ደግሞ ለዲጂታል ኢኮኖሚው የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል በማፍራት የቴክኖሎጂ ፈጠራና የዲጂታል ሥራ ዕድል እድገትን ያፋጥናል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዩኒቨርሲቲና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ልማት ተቋማት የወደፊቱን የእውቀትና የፈጠራ አቅም ለመገንባት ወሳኝ ሚና ይኖራቸዋል። በተመሳሳይም የሳይበር ደህንነት ሥርዓት የዲጂታል ኢኮኖሚውን ከስጋቶች የሚጠብቅ፣ የመረጃ ደህንነትንና የሀገር ዲጂታል ሉዓላዊነትን የሚያስከብር ጠንካራ ጋሻ ሆኖ ይቀጥላል። በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽንና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፎች ኢትዮጵያ እየወሰደች ያለችው መዋቅራዊ እርምጃ የአገር ውስጥ አገልግሎቶችን ከማዘመንና የዜጎችን ኑሮ ከማቅለል ባለፈ፣ ሀገሪቱን በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ፣ አካታችና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ኢኮኖሚ ባለቤት ለማድረግ የሚያግዝ ነው። ኢትዮጵያ አዲስ የተስፋ አድማስ፡- '’ኢትዮጵያዊነት ያስተማረን ትልቁ እውነት፤ በጊዜያዊ ፈተናዎች ተሸንፎ መውደቅ ሳይሆን፣ ችግሮችን ወደ ዕድል፣ ፈተናዎችንም ወደ ስኬት መለወጥና ድልን መቀዳጀት ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ያስመዘገባቸው ውጤቶች ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ቀጣይ የልህቀት ጉዞ ጠንካራ መነሻና መሠረት ይሆናሉ። በመሆኑም ኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታዋን ለማፋጠን በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተጀመሩ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተቀናጀ መንገድ በጋራ ገቢራዊ ማድረግ ይጠበቅባታል። ዲጂታል ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የእውቀት፣ የፈጠራና የተወዳዳሪነት ሀገራዊ መሠረት ነው።      
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 11635
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 21473
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 14500
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 20251
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 103902
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 78793
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57384
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 54962
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 39382
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 39177
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 38658
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 37316
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 103902
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 78793
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 57384
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 54962
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
በምክክር እንጂ በመሳሪያ ድምጽ ሀገር አይገነባም
Aug 8, 2026 324
ኢትዮጵያ የዛሬ ማንነቷና ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እዚህ እንድትደርስ በርካታ ውጣውረዶችን አልፋለች። በቀደመ ታሪኳም ዜጎች በራሳቸው የውስጥ ጉዳይ መስማማት ባለመቻል እርስ በእርስ ካደረጓቸው ግጭቶች ባለፈ የውጭ ሃይሎችም የራሳቸውን አሉታዊ ጫና ሲፈጥሩ ቆይተዋል፤ አሁንም ይህንኑ ለማስቀጠል ተላላኪዎቻቸውን ለመጠቀም ሲሞክሩ ይታያል። በአንድ ሃገር ውስጥ የማያግባቡ ጉዳዮች በየትኛውም አጋጣሚና የታሪክ ምዕራፍ ሊያጋጥሙ ይችላሉ። እነዚህን ችግሮች በሃይል ለመፍታት የሚደረገው የመሳሪያ ትንቅንቅ ግን አክሳሪና ዘመን እያለፈበትም ነው። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ሰላማዊ የእድገት ጉዞ ለማወክ የህዝቦቿን አንድነት ለመበጥበጥ ከቅርብም ሆነ ከሩቅ የሚመጡ ጠላቶች ጠፍተው አያውቁም። በየዘመናቱ የተሻገርናቸው የታሪክ ስብራቶችን ፣ የመብት ጥያቄዎችንና ሌሎችንም መነሻ በማድረግ በውስጥ ባንዳዎች እና በውጭ ባዳዎች አማካኝነት የማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ለመክተት፣ የብልጽግና ጉዞዋን ለማደናቀፍ የሚደረጉ ሴራዎች ዛሬም ላይ ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት ተሰሚነትና ተጽዕኖ የሚያሳምማቸው ለዜጎቿን እኩል ተጠቃሚነትና ብልጽግና መረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚያስጨንቃቸው እነዚህ ሃይሎች በመብት ፣ በነጻነት፣ በዴሞክራሲ፣ በማንነትና በሌሎችም የሃሰት ትርክቶች መነሻነት በሩቅ ቢያቅታቸው በቅርብ የውስጥ ተላላኪ ባንዳዎችን እያደራጁ በጀት መድበው የጦር መሳሪያ አቅርበው ሀገር የማፍረስ ሙከራቸውን አላቋረጡም። በመደመር እሳቤ ሁሉንም በአንድ ላይ በማቀራረብና የጋራ ትርክቶችን በመገንባት ከልዩነት ይልቅ የሚያቀራርቡ ጉዳዮች ላይ በማተኮር ዘላቂ ልማቷን መፃኢ ብሩህ ተስፋዋን ለማለምለም በሁሉም ዘርፍ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ተሳትፎ እየሰራች መሆኗም ምቾት ነስቷቸዋል። በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሔደ ያለውና ወርቃማው እድል ሃገራዊ ምክክር ልዩነቶችን በምክክር ለመፍታት ፣ የሚያስችሉ ወሳኝ ምዕራፎች ላይ ደርሷል ። በዚህ የምክክር ሒደት በሀገሪቱ የትኛውም ጥግ ያለ ዜጋ እንዲሁም በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የተወከሉበት ፣ የብሔር፣ የፖለቲካ አመለካከትና የሃይማኖት ልዩነት የማያደናቅፉት ሁሉንም ያሳተፈ ምክክር እየተካሔደ ይገኛል። ጥያቄያችንን በጠብመንጃ አፈሙዝ እንፈታለን ያሉ ታጣቂዎችም ብረት በማስቀመጥ አጀንዳዎቻቸውን ይዘው ወደ ጠረጴዛው ቀርበዋል። ልክ ናቸው ሀገር ከሁሉም ነገር ትበልጣለችና ይሄንን ወርቃማ እድል ለመጠቀም ማሰብ ትክክለኛው ውሳኔ ነው። በትጥቅ ትግል ጥያቄያችንን እንመልሳለን በሚል ሽፋን የሌሎችን አጀንዳ ለማሳካት የሚደረግ ጥረት የሃገርና የትውልድ ጠባሳ ከማስቀመጥና የታሪክ ተወቃሽ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው መገንዘብ ብልህነት ነው። የዚህ ምክክር ተሳታፊ/ተመካካሪ ከሆኑት የቀድሞ ታጣቂዎች መካከል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) አመራር ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በዚህ ይስማማሉ ። ሀገራዊ ምክክር ትልቅ ተስፋ የጣልንበት፣ በንግግር፣ በምክክር ሀገራችንን የምናስቀጥልበት፣ ሁሉም ተነጋግሮ ተመካክሮ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ከችግሮች ነፃ የሚያደርግበት ነው ይላሉ። ምክክሩ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚነጋገርበት፣ የሚመካከርበት እና በሃሳብ የበላይነት ጠንካራ ሃገር የሚፈጠርበት መልካም የታሪክ አጋጣሚ መሆኑንም ይናገራሉ። በምክክር፣ በድርድር የሕዝብን ጥያቄ በመመለስ ሀገርን የምናስቀጥልበትና የውጭ ኃይሎችን ጣልቃ ገብነት የምናስወግድበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ነው ብለዋል። የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራር የቀድሞ ታጣቂ ጃል ሰኚም ይሄንኑ ሃሳብ ይጋራሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ለዓመታት የቆዩ ልዩነቶችን ለመፍታት ሀገራዊ ምክክር መዘጋጀቱ ትልቅ እርምጃ እንደመሆኑ እሳቸውም ያላቸውን ሀሳብ በማንጸባረቅ እየመከሩ ይገኛሉ። እርሳቸውና ቡድናቸው ከዚህ ቀደም የትጥቅ ትግልን በመምረጥ ጫካ ገብተው እንደነበር አስታውሰው፤ ችግሮችን በመሳሪያ ከመፍታት ይልቅ በሰላማዊ የምክክር መድረክ መፍታት ጥሩ አማራጭ መሆኑን አምነው ወደ ሰላም መንገድ መምጣታቸውንም ተናግረዋል። ችግሮቻቸውን በምክክር የፈቱ ሀገራት በሁሉም ዘርፍ ዕድገታቸውን የሚያስቀጥሉ ሲሆኑ ወደ ትጥቅ ትግል ያመሩና ግጭት ውስጥ የገቡት ደግሞ በፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውድቀት ለከፋ ድህነት መዳረጋቸውን ጠቅሰዋል። የጦር መሣሪያ በመነቅነቅና ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ በመግባት የሚፈታ ችግር እንደሌለ የሚናገሩት ደግሞ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ(አብን) አመራሩ ተመካካሪ ጣሒር መሀመድ ናቸው። ጫካ ባለውና እዚህ ባለው ሰው መካከል ምንም ዐይነት የዜግነት ልዩነት እንደሌለ ገልጸው ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሃሳብ ለመታገል ልዩነቱን ለማቅረብ የፈለገ ሁሉም ዜጋ በምክክሩ የመሳተፍ ነጻነት እንዳለው ገልጸዋል። በሃገራዊ ምክክሩ ከትጥቅ ትግል ይልቅ በሰላማዊ መድረክ መወያየት የተመረጠበት ዋና ምክንያት ዘላቂ ሰላም፣ አገራዊ መግባባት እና የፖለቲካ ባህል ለውጥ ለማምጣት ነው:: የትጥቅ ትግል የዜጎችን ህይወት ያጠፋል፣ መሰረተ ልማቶችን ያወድማል፤ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድቀትንም ያመጣል: ፤ ሰላማዊ መድረክ ግን ያለምንም ደም መፋሰስ ሃሳብን በሃሳብ ለመሞገት እድል ይሰጣል:: በኃይል የሚመጣ ለውጥ ብዙውን ጊዜ አሸናፊና ተሸናፊን ስለሚፈጥር የቁስል እና የቂም ዑደትን ያስቀጥላል:: በሰላማዊ ውይይት የሚገኝ መፍትሄ ግን የሁሉንም ወገን ስጋት እና ፍላጎት ያገናዘበ በመሆኑ ዘላቂነት ይኖረዋል:: ሃገራዊ ምክክሩ የታጠቁ አካላትም ጭምር መሳሪያቸውን አስቀምጠው በሃሳብ እንዲፎካከሩ መንገድ ከፍቷል። ይህ ታሪካዊና ወርቃማ እድል ኢትዮጵያዊንን አግባብቶ ወደተረጋጋችና የበለጸገች ሃገር የሚመራ በመሆኑ ስኬታማነቱ አያጠራጥርም። ለእድለኛው ትውልድ ያጋጠመው ወርቃማው ስጦታ ሃገራዊ ምክክር የተቋቋመለትን ዓላማ ያሳካል።
ከካይሮ ሴራ ጀርባ፤ የCNN ዘገባ የገለጠው የኢትዮጵያ እውነት
Aug 4, 2026 1215
ግብፅ በታሪኳ የዓባይን ወንዝ በብቸኝነት ለመጠቀም የተከተለችው ዋና ስልት "ጠንካራና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለካይሮ ስጋት ናት" የሚል ቀመርን ነው። በመሆኑም በየዘመናቱ የተነሱ የካይሮ መንግስታት ኢትዮጵያ ተረጋግታ ሀብቷን እንዳታለማ ለማድረግ ረዥም ርቀት ተጉዘዋል። በታሪክ አጋጣሚ የዓባይን መነሻ ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር በርካታ የወረራ ሙከራዎችን ያደረገችው ግብጽ፣ በጉንደት (1875) እና በጉራዕ (1876) በተደረጉ ታሪካዊ ውጊያዎች በኢትዮጵያውያን ጠንካራ ክንድ መራራ ሽንፈትን አስተናግዳለች። ከቀጥታ ጦርነት ከተመለሰች በኋላ ካይሮ ስልቷን ወደ "ውስጥ ለውስጥ ማበጣበጥ" ቀይራለች። ይህም የኢትዮጵያን መንግስት ትኩረትና የፋይናንስ አቅም ከልማት ፕሮጀክቶች (በተለይም ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና መሰረተ ልማቶች) ወደ ጸጥታ ማስከበር እንዲዞር ለማድረግና ሀገሪቱን ወደማያልቅ የውስጥ ብጥብጥ ለመክተት በርካታ ሴራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። ይህ አልሳካ ሲላት ደግሞ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨትን እንደ አማራጭ መንገድ ስትጠቀም ቆይታለች፤ እየተጠቀመችም ትገኛለች። የግብፅ የፖለቲካ ምሁራንና ዲፕሎማቶች የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ “ግድቡ በታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ላይ የከፋ ጉዳት ያደርሳል” በሚል የሐሰት ትረካቸውን ሲያሰራጩና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ሲያሳስቱ ቆይተዋል። ሆኖም ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥበብ የተሞላበት አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ የውጭ ተፅዕኖዎችንና የውስጥ ፈተናዎችን በመሻገር ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት ከፍፃሜ ማድረስ ችላለች። ይህም የመደመር እሳቤ የሆነው ፈተናን ወደ እድል የመቀየር ትልቁ ማሳያ ነው። የግድቡን እውን መሆን ተከትሎም የካይሮ ተደጋጋሚ የሀሰት ቅሬታና የተዛባ ፕሮፓጋንዳም ዘግይቶም ቢሆን እውነቱ በዓለም ፊት እየተገለጠ ይገኛል።በCNN “Connecting Africa” ወርሃዊ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ ያቀረበችው ዘገባ የዚሁ እውነት ማሳያ ነው። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 የቢቢሲ የኮምላ ዱሞር ሽልማት አሸናፊ የሆነችው ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት ጉባ ተገኝታ ባከናወነችው ዘገባ የካይሮን ምናባዊ ቅዥት የሚያፈርሱ ተግባራዊ እውነቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጋለች። የምህንድስና ልህቀት እና የጋራ ልማት ማሳያ፦ CNN በዘገባው ስለ ሕዳሴ ግድብ ለዓመታት ሲነገር የቆየውን የሀሰት ሴራ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምህንድስናና የግንባታ ባለሙያ ኢትዮጵያዊያን ጥረትን እውን ያደረገ የኢንጂነሪንግ ልህቀት አብነት መሆኑን አጉልቶ አሳይቷል። የግብፅ መንግስት ግድቡን “የስጋት ምንጭ” አድርጎ ለማሳየት ቢጥርም፣ የCNN ዘገባ ግን ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው የተዘረጋ የጋራ እድገት መድረክ መሆኑን አብራርቷል። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 2025 በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ህይወት እያበራ መሆኑን በማሳየትም፤ ግድቡ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን በተግባር ገልጧል። የጋዜጠኛ ሩባዲሪ ዘገባ የግብፅን ተደጋጋሚ ቅሬታና ሴራ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች ውድቅ ያደርጋል። የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ፦ ግድቡ የታችኞቹን የተፋሰሱ ሀገራት የማይጎዳ፣ ይልቁንም የውሃ ፍሰትን በማስተካከልና ደለልን በመቀነስ ረገድ አዎንታዊ ሚና የሚጫወት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሰረተ ፕሮጀክት መሆኑን የግድቡ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሃሳብን በማካተት ጭምር አሳይታለች። ቀጣናዊ የመደመር እሳቤ ማሳያ ፦ ግድቡ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በመሸጥ ገቢ ከማግኘቷም ባለፈ፣ የቀጣናውን ሀገራት በኃይልና በኢኮኖሚ የሚያስተሳስር ነው። ይህ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግስት እሳቤ ማለትም “በጋራ ማደግ እና እርስ በእርስ መደጋገፍ” የሚለውን ቀጣናዊ ራዕይ በተግባር የሚያረጋግጥ እንጂ ግብፅ እንደምትለው ቀጣናውን ወደ አለመረጋጋት የሚከት አለመሆኑን ያመላክታል። ሰው ተኮር የኢኮኖሚ ሽግግር፦ በCNN ዘገባ የተካተቱት የኢንተርናሽናል ግሮውዝ ሴንተር (IGC) የኢትዮጵያ ኃላፊ ቴዎድሮስ መኮንን በግልጽ እንዳስቀመጡት፤ 70 በመቶው ህዝቧ ከ30 ዓመት በታች የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ከ15 ዓመታት በፊት ከነበረችበት ከአማካይ በታች የነበረ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁን በአፍሪካ ከሚገኙ ግዙፍ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት አንዷ መሆን ችላለች። ግድቡም ይህንን ወጣት ኃይል ወደ ዘላቂ ምርታማነት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት አካል ነው። መደምደሚያ፦ በአጠቃላይ ግብፅ ግድቡን መሰረት በማድረግ የምታካሂደው የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የፖለቲካ ቁማር እንጂ ከሳይንሳዊና መሬት ላይ ካለው እውነት ጋር እንደማይገናኝ የCNN ዘገባ በግልጽ አሳይቷል። በሀገር ውስጥ አቅም እና በጥበብ በተሞላ ሀገራዊ አመራር እውን የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ጊዜ የሚቀርጽ፣ የአፍሪካ ቀጣናን በኃይልና በንግድ የሚያስተሳስር የልማት ማማ እንጂ የትኛውንም ሀገር የሚጎዳ ስጋት አይደለም። የመደመር እሳቤ ያጎናፀፈው ይህ የታሪካዊ ድል ብርሃንም መላውን ቀጣና ማብራቱን ቀጥሏል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም