ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በምስራቅ ጎጃም ዞን በመስኖ ከለማው መሬት እሰካሁን ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል
Mar 26, 2026 18
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን በያዝነው በጋ በአንደኛው ዙር በመስኖ ከለማው መሬት ላይ እስካሁን ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ኃላፊ አቶ አበበ መኮንን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከለውጡ ወዲህ በምግብ ራስን ለመቻል የመስኖ ልማት አንዱ አማራጭ ተደርጎ እየተሰራ ይገኛል። በበጀት ዓመቱም በአንደኛው ዙር ከ41 ሺህ 300 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ሰብል በመሸፈን ከ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አውስተዋል። ከ125 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከለማው 41 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እስካሁን ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል። የተጠቀሰውን ያህል ምርት መሰብሰብ የተቻለውም ቀድመው ከደረሱ ገብስና የተለያዩ የጓሮ አትክልቶች መሆኑን ጠቁመው ቀሪውን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የመስኖ ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግም ከ84 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘርና ከ9 ሺህ 700 በላይ የውሃ መሳቢያ ፓምፖች ጥቅም ላይ መዋላቸውን አስረድተዋል። በዞኑ የአዋበል ወረዳ የሰንበት ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጌታሁን ይርሴ እንደገለጹት በመስኖ ልማት በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ በማምረት ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት በመስኖ ካለሙት መሬት 10 ኩንታል ስንዴና 20 ኩንታል የጓሮ አትክልት ማግኘታቸውን አውስተው ዘንድሮ ከዚህ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል። በዚሁ ወረዳ የወጀል ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ይከበር ነጋ በበኩላቸው በያዝነው በጋ ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን በመስኖ ልማት መሸፈናቸውን አስረድተዋል። በየዓመቱ ከመስኖ ልማት የሚገኘውን ምርት በመሸጥ ከ60 ሺህ ብር በላይ ገቢ እንደሚያገኙ አውስተው ዘንድሮም ከዚህ የበለጠ ገቢ እንደሚያገኙ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።    
የምርጫ ካርድ በመውሰድ በድምፃችን የሚመራንን ፓርቲ ለመወሰን ተዘጋጅተናል
Mar 26, 2026 30
ደብረ ማርቆስ ፤መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ) ፡-የምርጫ ካርድ በመውሰድ በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የበኩላቸውን ለመወጣት የሚሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን ተወስኖ፣ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ስም እንዲሁም የመለያ ምልክት አደራደር ቅደም ተከተል ለመወሰን የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት አካሒዷል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም ፖሊሲና ስትራቴጂያቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የምርጫ ክርክርና ቅስቀሳ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም በአማራ ክልል ደብረ ማርቆስ ከተማና አካባቢው አጠቃላይ ምርጫውን በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር በየምርጫ ጣቢያዎቹ ተዘዋውሮ የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ያሉ ዜጎችን አነጋግሯል። ከየምርጫ ጣቢያዎቹ አስተያየት የሰጡ ነዋሪዎችም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በከተማው ቀበሌ 11 የሚኖሩትና የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኘናቸው ወይዘሮ ውባለም ዝይን፤ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የመምረጥ እድል ያገኙ መሆኑን ተናግረው ካርድ በመውሰድ ለምርጫው ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመገናኛ ብዙሃን የሚካሄዱ የፓርቲዎችን የክርክር መድረኮች እየተከታተሉ መሆኑን አንስተው ለሀገርና ህዝብ ይበጃል ለሚሉት ፓርቲ ድምፃቸውን እንደሚሰጡም ነው የሚናገሩት። የቀበሌ 10 ነዋሪ የሆኑት አቶ አንተነህ ይርዳው፤ በአምስት አመት አንዴ የሚገኘውን እድል በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመጠቀም የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ጉዳይ የህዝብ የመወሰን መብት የሚረጋገጥበት መልካም አጋጣሚ በመሆኑ ከወዲሁ የምርጫ ካርድ በመውሰድ እድሉን መጠቀም ይገባል ብለዋል። በመሆኑም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ምርጫ ከወዲሁ ካርድ በመውሰድ በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ትግስት ዳኘ፤ የመራጭነት ካርዳቸውን በመያዝ ድምፃቸውን ለመስጠት ከወዲሁ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ሂደት የዜጎች ተሳትፎ የሚረጋገጥበትና ሀገራዊ ሃላፊነትን የመወጣት ሚና በመሆኑ ለመምረጥ የሁላችንም ዝግጁነት ያስፈልጋል ብለዋል። የምርጫ ካርድ ከመያዝ በተጓዳኝ ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የበኩላቸውን ለመወጣት የሚሰሩ መሆኑን አስተያየት ሰጭዎቹ ገልጸዋል።
አገልግሎቱ 500 ሺህ ስማርት የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን የመግጠም ሥራ እያከናወነ ነው
Mar 26, 2026 68
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ 500 ሺህ ስማርት የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን ለነባርና አዲስ ደንበኞቹ የመግጠም ሥራ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር ለኢዜአ እንዳሉት፤ በፕሮጀክቱ 125 ሺህ ስማርት ሶስት ፌዝ፣ 25 ሺህ ስማርት ነጠላ ፌዝ እንዲሁም 350 ሺህ ኦፍላይን (Semi-Smart) ነጠላ ፌዝ ዘመናዊ የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን የመግጠም ሥራ እየተከናወነ ነው። እስካሁን በተከናወነው ሥራ 60 ሺህ 457 ነጠላ ፌዝ ቆጣሪዎችን እስከ 7 ነጥብ 5 ኪሎ ዋት ድረስ ኃይል ለሚጠቀሙ ለመኖሪያና ለንግድ ደንበኞች መገጠማቸውን አስረድተዋል። በተጨማሪም 7 ሺህ 13 ባለ ሦስት ፌዝ ቆጣሪዎች ከ8 እስከ 24 ኪሎ ዋት ድረስ ኃይል ለሚጠቀሙ ለመኖሪያ፣ ለንግድና ለአነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ተገጥመው አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህ ዘመናዊ ቆጣሪዎች የቅድመ ክፍያ ደንበኞች ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ሳይሄዱ የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ቶክን ቁጥር በመግዛት የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲሞሉ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል፡፡   ስማርት የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን ለነባርና አዲስ ደንበኞች የመግጠም ሥራው እየተከናወነ የሚገኘው በ48 ነጥብ 8 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ መሆኑንም አስታውቀዋል። ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ከ67 ሺህ በላይ ደንበኞች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በኢትዮ ቴሌኮምና በአዋሽ ባንክ የሞባይል አፕሊኬሽኖች በሳምንት ሰባቱንም ቀናት 24 ሰዓት የትም መሄድ ሳይጠበቅባቸው ቤታቸው ሆነው የኤሌክትሪክ ኃይል መግዛት እንዲችሉ ዕድል ፈጥሯል ነው ያሉት፡፡ ይህ ፕሮጀክት ቀደም ሲል የነበሩ የቅድመ ክፍያ ካርድ መጥፋት፣ የካርድ መበላሸት፣ የኔትዎርክ መቆራረጥ እንዲሁም ቆጣሪው ላይ ብር አልገባልኝም የሚሉትን ችግሮች ይቀርፋል ሲሉም አረጋግጠዋል። በተጨማሪም ከፍተኛ በሆነ ኃይል መጨመር (Over voltage) ምክንያት የሚመጣን የንብረት አደጋ ይከላከላል፣ ደንበኞች በሚሰጣቸው መሳሪያ አማካኝነት ፍጆታቸውን መከታተል በመቻላቸው አጠቃቀማቸውን መቆጠብ እና ወጪ እንዲቀንሱ ያስችላቸዋል ነው ያሉት፡፡  
ወደ ዓለም ዋንጫ የሚያልፉ ቀሪ ስድስት ሀገራት የሚለዩባቸው የማጣሪያ ጨዋታዎች 
Mar 26, 2026 74
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ 23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ ጣምራ አዘጋጅነት ከሰኔ 4 እስከ ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። በዓለም ዋንጫው 48 ሀገራት የሚሳተፉ ሲሆን፤ እስከ አሁን 42 ሀገራት የተሳትፎ ትኬታቸውን ቆርጠዋል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ቀሪ ስድስት ሀገራት የሚለዩባቸው የመጀመሪያ ዙር የማጣሪያ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ።   የዓለም ዋንጫ የአውሮፓ ጥሎ ማለፍ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ይከናወናሉ። ምሽት 2 ሰዓት ላይ ቱርክዬ ከሮማንያ በቱፕራስ ስታዲየም ይጫወታሉ። የአራት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ጣልያን ከሰሜን አየርላንድ፣ ዴንማርክ ከሰሜን ሜቄዶኒያ፣ ፖላንድ ከአልባኒያ፣ ቼክ ሪፐብሊክ ከአየርላንድ፣ ዩክሬን ከስዊድን፣ ስሎቫኪያ ከኮሶቮ እና ዌልስ ከቦሲኒያ እና ሄርዞጌቪና በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ከ45 ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፉ ሀገራት ለዓለም ዋንጫው ለማለፍ ወደሚደረገው የመጨረሻ ማጣሪያ ያልፋሉ። በመጨረሻው ማጣሪያ የጣልያን እና ሰሜን አየርላንድ አሸናፊ ከዌልስ እና ቦሲኒያና ሄርዜጎቪና አሸናፊ፣ የፖላንድ እና አልባኒያ አሸናፊ ከዩክሬንና ስዊድን አሸናፊ፣ የቱርክዬና ሮማኒያ አሸናፊ ከስሎቫኪያና ኮሶቮ አሸናፊ እንዲሁም የዴንማርክ እና ሰሜን ሜቄዶኒያ አሸናፊ ከቼክ ሪፐብሊክ እና አየርላንድ አሸናፊ ጋር ይጫወታሉ። የመጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጨዋታዎችን የሚያሸንፉ አራት ሀገራት ለዓለም ዋንጫ ማለፋቸውን ያረጋግጣሉ። አራቱ ሀገራት አስቀድመው በቀጥታ ወደ ዓለም ዋንጫ ያለፉ 12 የአውሮፓ ሀገራትን ይቀላቀላሉ። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከአውሮፓ 16 ሀገራት ይሳተፋሉ። በተያያዘም የክፍለ አህጉራት የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ ጨዋታዎችም ይካሄዳሉ። በማጣሪያው ላይ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (አፍሪካ)፣ ኢራቅ (እስያ)፣ ቦሊቪያ (ደቡብ አሜሪካ)፣ ሱሪናም (ሰሜን/ማዕከላዊ አሜሪካ እና ካሪቢያን)፣ ጃማካይ (ሰሜን/ማዕከላዊ አሜሪካ እና ካሪቢያን) እና ኒው ካሌዶኒያ (ኦሽንያ) ይሳተፋሉ። በፊፋ የሀገራት የእግር ኳስ ደረጃ የተሻለ ደረጃ ያላቸው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (48ኛ) እና ኢራቅ (55ኛ) በቀጥታ ወደ መጨረሻው የማጣሪያ ጨዋታ አልፈዋል። ቀሪዎቹ አራት ሀገራት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታቸውን በሜክሲኮ ያደርጋሉ። ቦሊቪያ ከሱሪናም ከሌሊቱ 7 ሰዓት በስታዲዩ ቢቢቪኤ፣ ኒው ካሌዶኒያ ከጃማይካ በአክሮን ስታዲየም ከጠዋቱ 12 ላይ ይጫወታሉ። የኒው ካሌዶኒያ እና ጃማይካ አሸናፊ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ የቦሊቪያ እና ሱሪናም አሸናፊ ከኢራቅ ጋር ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታቸውን ያሸነፉ ሁለት ሀገራት ለዓለም ዋንጫው ያልፋሉ።
የመውረድ ስጋት ያለባቸው ክለቦች የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ 
Mar 26, 2026 66
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል። ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ ይርጋጨፌ ቡና ከአዲስ አበባ ከተማ በአበባ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ይርጋጨፌ ቡና በሊጉ ባደረጋቸው 20 ጨዋታዎች በሁለቱ አሸንፎ በ13ቱ ተሸንፎ በአምስቱ አቻ ወጥቷል። በ20ዎቹ ጨዋታዎች ዘጠኝ ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 31 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አዲስ አዳጊው ይርጋጨፌ ቡና በ11 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው አዲስ አበባ ከተማ በሊጉ 20 ጨዋታዎች አከናውኖ ሶስት ጊዜ ድል ሲቀናው፤ በ15ቱ ተሸንፏል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። 12 ግቦችን ሲያስቆጥር 41 ጎሎችን አስተናግዷል። አዲስ አበባ ከተማ በተመሳሳይ 11 ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ 13ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ይርጋጨፌ ቡና ባለፉት 12 የሊግ ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያስገኝለታል። በአንጻሩ አዲስ አበባ ከተማ ካሸነፈ ከወራጅ ቀጠና ይወጣል።   በሌላኛው መርሐ-ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከአርባምንጭ ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ድሬዳዋ ከተማ እስከ አሁን በሊጉ ማሸነፍ የቻለው ጨዋታ ብዛት ስድስት ነው። 11 ጊዜ ሲሸነፍ ሶስት ጊዜ አቻ ወጥቷል። 18 ግቦችን ሲያስቆጥር 31 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ21 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው አርባምንጭ ከተማ በበኩሉ 20 ጨዋታዎችን አድርጎ ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ፤ 14 ጊዜ ተሸንፏል። በአራት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 10 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 37 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አርባምንጭ ከተማ በ10 ነጥብ የመጨረሻውን 14ኛ ደረጃን ይዟል። ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት አምስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። አርባምንጭ ከተማ ባለፉት 13 ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። ጨዋታዎቹ ላለመውረድ በሚደረገው ፉክክር ወሳኝ የሚባሉ ናቸው።   ቦሌ ክፍለ ከተማ ከባህር ዳር ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ቦሌ ክፍለ ከተማ በ31 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ባህር ዳር ከተማ በ16 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ባለፉት አራት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ከድል የራቀው ቦሌ ክፍለ ከተማ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ባህር ዳር ከተማ ካሸነፈ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘግባል።
የሚታይ
በአዲስ አበባ ሕገ ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመግታት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Mar 25, 2026 278
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ሕገ ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመግታት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕግ ማስከበርና ቁጥጥር ንዑስ ኮሚቴ ባለፉት አራት ወራት ከአስራ አምስት ቀናት የሕግ ማስከበር እና የቁጥጥር ሥራዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል።   በውይይቱ ነዳጅን ጨምሮ በመዲናዋ የሸቀጦች ግብይትን ያለደረሰኝ የሚፈጽሙ ህገ ወጥ ነጋዴዎችና ሕገ ወጥ የደላላ እንቅስቃሴዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ የቀጣይ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊና የሕግ ማስከበርና ቁጥጥር ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሊዲያ ግርማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በመዲናዋ የሕገ ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመግታት የተሰሩ ሥራዎች ውጤት እያመጡ ነው። እንዲያም ሆኖ አሁንም ነዳጅን በጄሪካን ጨምሮ በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰቦች እጅ መኖሩን መለየቱን ገልጸው፤ ሕገ ወጥ የነዳጅ ዝውውር ላይ የሚደረገው ቁጥጥር ይበልጥ ይጠናከራል ብለዋል። ሰላምና ጸጥታ፣ ደንብ ማስከበር፣ የአዲስ አበባ ፖሊስና የንግድ ቢሮ ቅንጅታዊ አካሄድ ከበፊቱ በላቀ መልኩ ሊተገበር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። የቁጥጥር ሥራው በዘመናዊ መልኩ እንዲካሄድ ትኩረት መስጠት እንደሚገባም አመልክተዋል። የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ ተስፋዬ ደንድር በበኩላቸው፤ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተደረገ ቁጥጥርና ክትትል 50 ሺህ 942 ሊትር ናፍጣ በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር መያዙን ገልጸዋል። በተመሳሳይም 8 ሺህ 974 ሊትር ቤንዚን በቁጥጥር ሥር ውሏል ያሉት ኃላፊው፤ 35 ግለሰቦችም በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉን ተናግረዋል። ተሽከርካሪዎች ላይ ተጨማሪ ሳልቫቲዮ በመግጠም በሕገ ወጥ መንገድ ነዳጅ ማዘዋወር፣ የነዳጅ ማደያዎች አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች እንዲሁም የቁጥጥር ሥራው ወጥ አለመሆን በውስንነት ከሚጠቀሱ ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል እንደሚገኙበት አብራርተዋል።   የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደገለጹት፤ በአዲስ አበባ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት የለም። እጥረቱ ሰው ሰራሽ ነው ያሉት ኃላፊዋ፤ በምሽት የሚሸጥ ነዳጅ ላይ የተቀናጀና ጠንካራ የቁጥጥር ሥራ ይጠይቃል ብለዋል። የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮም በሕገ ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ ነዳጅ አቅራቢዎች ወደ ሕጋዊ መስመር እንዲገቡ የማወያየት ሥራዎች በሰፊው እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ጠቅላይ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድ እንደተናገሩት፤ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴን ለመግታት ዘላቂው መንገድ በሕገ ወጥ ተግባር ላይ የሚሰማሩትን ግንዛቤ በማስጨበጥ መመለስ ነው።   ሕግን አለመዋቅ ከተጠያቂነት አያድንም ያሉት ምክትል ኮሚሽነሩ፤ በሕገ ወጥ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ወደ ሕጋዊ መስመር ሊገቡ እንደሚገባም አሳስበዋል። የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጥበቡ ደጀኔ (ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ ተጨማሪ ሳልቫቲዮ የተገጠመላቸው ተሽከርካሪዎች በሕገ ወጥ መንገድ ነዳጅ እንደሚያዘዋውሩ በቁጥጥርና ክትትል ተለይቷል። ቁጥጥሩ ከነዳጅ ማደያዎች ባለፈ ተሽከርካሪዎች ላይ ሊደረግ እንደሚገባ ገልጸው፤ መንደሮች ውስጥም ጭምር በተጠናከረ መልኩ ሊካሄድ ይገባል ብለዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ምክትል መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ዳንኤል ጥላሁን እንደገለጹት፤ በክፍለ ከተማው ነዳጅ ማደያዎች በአግባቡ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ክትትል እየተደረገ ነው።
በአማራ ክልል አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት እየሰፈነ ነው-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 
Mar 25, 2026 440
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአማራ ክልል ሰላምና መረጋጋት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል ያለውን ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸው በክልሉ ሰላምና መረጋጋት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየ መሆኑን ገልፀዋል። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች፣ከከተሞች እስከ ገጠር ባደረጉት የመስክ ምልከታ የክልሉ ሰላም መሻሻል ማሳየቱን ገልጸዋል። በክልሉ ያለው ሁኔታ ቀደም ሲል በማህበራዊ ሚዲያዎች ከሚነገረው በተለየ መልኩ እጅግ የተረጋጋ መሆኑን ገልጸዋል። አሁን ያለው ችግር ከፀጥታ ስጋት ይልቅ የአስተሳሰብ ግድፈትና በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሱ መረጃዎች የፈጠሩት የስነ-ልቦና ጫና መሆኑን ጠቁመዋል። ቁጥራቸው በዛ ያሉ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ ተቀላቅለው ሰላማዊ ህይወት መጀመራቸውን ገልጸዋል። በተለይም የታጣቂ አመራር አባላት የተከናወኑ የልማት ስራዎችን እንዲጎበኙ መደረጉን አንስተዋል። በዚህም ታጣቂዎቹ የልማት ስራዎችን የመደገፍ ተነሳሽነት እንደፈጠረላቸው ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት በክልሉ እጅግ የሚያስደንቁ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተው፤ የክልሉ መንግስትና የፀጥታ ኃይሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ እየተጠናከሩ መምጣታቸውንም አክለዋል።
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ መሆን የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Mar 25, 2026 322
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ መሆን የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ዜጎች ለኢትዮጵያ ይጠቅማል የሚሉትን ለመምረጥ አስቀድመው የምርጫ ካርዳቸውን እንዲወስዱም ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፅ በሚሰጥበት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ይገኛል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በምርጫ ዝግጅት መልዕክታቸው፤ ስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሕዊና ገለልተኛ ሆኖ መጠናቀቁ የህዝብ ተቀባይነት ማስገኘቱን አስታውሰዋል። ብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ አግኝቶ በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር ለተፎካካሪ ፓርቲዎች የመንግስት ኃላፊነት በመስጠት አስቻይ የፖለቲካ ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የተፈጠረው ጤናማ የፖለቲካ ምኅዳርም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላት በሀገር ሰላም፣ ልማትና ዕድገት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። ፓርቲው ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ የሚበጁ አማራጭ ሃሳቦቻቸውን በነጻነት እንዲያቀረቡ ጽኑ ፍላጎት እንዳለው አንስተዋል። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅም መከበርን በተመለከተ የማይናወጥ አቋም ሊኖራቸው እንደሚገባም አመልክተዋል። ለዚህም የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ተሞክሮዎችን በመቀመር ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በውጤታማነት ማካሄድ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። የብልፅግና ፓርቲም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባስመዘገባቸው ተጨባጭ ውጤቶች ብቻ በህዝብ ተመራጭ መሆን የሚሻ ፓርቲ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ ፍትሐዊና መልክዓ-ምድራዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም የትውልድና የብሔራዊ ጥቅም አንጓ መሆኑን መገንዘብ እንደሚገባ አስረድተዋል። የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ የህዝብን አንድነት ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረትም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር የመስራት ባህልን ማጎልበት እንደሚኖርባቸው አንስተዋል። በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያለው መንግስት ለመመስረት የምርጫው ዴሞክራሲዊነት ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን በመገናኛ ብዙሃን ለህዝቡ እያዳረሱ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዜጎችም ድምፅ መስጫ ካርድ መውሰድ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ሰላማዊ፣ ተዓማኒና የህዝብ ተቀባይነት እንዲኖረው ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ፈጣን የልማት ዕድገት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ የማስረከብ ትልም ፍሬ እያፈራ መሆኑን የሚያሳይ ነው
Mar 25, 2026 200
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስደናቂ የልማት ዕድገት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ የማስረከብ ትልም ፍሬ እያፈራ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጣሊያን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ምክትል ሚኒስትር ማሪያ ትሪፖዲ፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ እና ተጋባዦች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመዲናዋ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ የልማት ስኬቶች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻነትን እያሳደገ ነው። የዓለም ሶስተኛዋ የዲፕሎማሲ ማዕከል የአፍሪካ መዲናና ውቧ አዲስ አበባ የአህጉሪቷ የመግቢያ በርነትን በፍጥነት እያሳደገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የአዲስ አበባን ምቹና ተወዳዳሪነት ለማሳለጥ በተገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ውስጥ የነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ቅድሚያ እንደተሰጠው አስረድተዋል። በመዲናዋ በመሠረተ ልማት መስክ የተመዘገቡ ውጤቶችም የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ትልም ፍሬ እያፈራ መሆኑን ያሳያል ብለዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የአገልግሎት አሰጣጠን ለማሳለጥ የተወሰዱ ርምጃዎች ኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት የስበት ማዕከል እያደረጋት እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡ የአዲስ አበባ የአዲስ መሶብ የዲጂታል የአንድ ማዕከል ለአልሚ ባለሃብቶች የተሳለጠ የመንግስት አገልግሎት የሚያገኙበትን አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩንም ገልጸዋል። የአዲስ አበባን ፈጣን ዕድገት በማሳለጥ ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢን በመፍጠር የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ እያበረታታ መሆኑን አንስተዋል። የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም የመዲናዋን የኢንቨስትመንት አማራጮች ለማሳየት ገንቢ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያና ጣሊያን ወዳጅነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳጅነትም የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብርን በማጠናከር ከፍተኛ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ አንስተዋል። በንግድና ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚ ባለሃብቶች ድጋፍና ትብብር እንደሚደረግ ጠቅሰው፤ የጣሊያን ባለሃብቶች ዕድሉን እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በባሕር ዳር እና ጎንደር እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ከተሞቹን ወደ ላቀ ዕድገት የሚያሸጋግሩ ናቸው
Mar 25, 2026 153
አዲስ አበባ፤መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡-በባሕር ዳር እና በጎንደር ከተሞች እየተከናወኑ የሚገኙ መጠነ ሰፊ የልማት ስራዎች፣ከተሞቹን ወደ ላቀ የእድገት ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በሁለቱ ከተሞች የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሥፍራው ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ፤ጉብኝቱ ቀደም ብለው የተጀመሩ ግዙፍ ስራዎች ያለሙትን ግብ ማሳካታቸውን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በባሕር ዳር ከተማ ጣናን ለዕይታ ግልጽ የሚያደርገው የኮሪደር ልማት የመጀመሪያ ምዕራፍ በስኬት መጠናቀቁን ጠቁመው፤ይህም ልማት ከውበት ባለፈ የከተማዋን የአየር ሁኔታ የቀየረ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከመሠረተ ልማት ዝርጋታ አኳያ የብስክሌት፣የአስፋልት እና የእግረኛ መንገዶች ግንባታ መጠናቀቁን ጠቅሰው፤ በመንገዶቹ ግራና ቀኝ የገበያ ማዕከላትን የመገንባት ስራ በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። በስፖርት ዘርፉም የሶስት ትልልቅ እግር ኳስ ሜዳዎች ግንባታ በዚህ ዓመት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ጠቅሰው፥እየተገነቡ ያሉ የቱሪስት መዳረሻዎችና የመዝናኛ ስፍራዎች የከተማዋን እድገት ይበልጥ እንደሚያፋጥኑም አረጋግጠዋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በጎንደር ከተማ ባደረጉት ጉብኝት፣ ከአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ጀምሮ ትልልቅ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። በተለይም በርካታ ቱሪስቶችና ምዕመናን የሚታደሙበት የጥምቀት ባህር አካባቢን የማልማት ስራ በፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ የገበያ ስፍራዎችና የስፖርት ማዘውተሪያዎች ግንባታ ጎን ለጎን የተለያዩ ታሪካዊ ቅርሶችን የማደስ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። እነዚህ ስራዎች አጠቃላይ የጎንደርን የቱሪስት ማዕከልነት ይበልጥ የሚያጠናክሩ ናቸው ብለዋል፡፡ ሌላኛው የጉብኝቱ አካል የነበረው የመገጭ ግድብ ግንባታውን በቀሩት የዓመቱ ወራት ለማጠናቀቅ የሚያስችል ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ግድቡ ጥራት ባለው ሁኔታ እየተገነባ መሆኑን መመልከታቸውን ገልጸው፤ በሂደቱ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል የተደራጀ የስራ ክፍፍል መደረጉን አመላክተዋል። ግድቡ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለአካባቢው ማህበረሰብ ዘርፈ ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎችን እንደሚያስገኝም አክለው ገልጸዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የምርጫ ካርድ በመውሰድ በድምፃችን የሚመራንን ፓርቲ ለመወሰን ተዘጋጅተናል
Mar 26, 2026 30
ደብረ ማርቆስ ፤መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ) ፡-የምርጫ ካርድ በመውሰድ በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የበኩላቸውን ለመወጣት የሚሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን ተወስኖ፣ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ስም እንዲሁም የመለያ ምልክት አደራደር ቅደም ተከተል ለመወሰን የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት አካሒዷል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም ፖሊሲና ስትራቴጂያቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የምርጫ ክርክርና ቅስቀሳ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም በአማራ ክልል ደብረ ማርቆስ ከተማና አካባቢው አጠቃላይ ምርጫውን በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር በየምርጫ ጣቢያዎቹ ተዘዋውሮ የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ያሉ ዜጎችን አነጋግሯል። ከየምርጫ ጣቢያዎቹ አስተያየት የሰጡ ነዋሪዎችም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በከተማው ቀበሌ 11 የሚኖሩትና የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኘናቸው ወይዘሮ ውባለም ዝይን፤ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የመምረጥ እድል ያገኙ መሆኑን ተናግረው ካርድ በመውሰድ ለምርጫው ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመገናኛ ብዙሃን የሚካሄዱ የፓርቲዎችን የክርክር መድረኮች እየተከታተሉ መሆኑን አንስተው ለሀገርና ህዝብ ይበጃል ለሚሉት ፓርቲ ድምፃቸውን እንደሚሰጡም ነው የሚናገሩት። የቀበሌ 10 ነዋሪ የሆኑት አቶ አንተነህ ይርዳው፤ በአምስት አመት አንዴ የሚገኘውን እድል በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመጠቀም የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ጉዳይ የህዝብ የመወሰን መብት የሚረጋገጥበት መልካም አጋጣሚ በመሆኑ ከወዲሁ የምርጫ ካርድ በመውሰድ እድሉን መጠቀም ይገባል ብለዋል። በመሆኑም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ምርጫ ከወዲሁ ካርድ በመውሰድ በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ትግስት ዳኘ፤ የመራጭነት ካርዳቸውን በመያዝ ድምፃቸውን ለመስጠት ከወዲሁ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ሂደት የዜጎች ተሳትፎ የሚረጋገጥበትና ሀገራዊ ሃላፊነትን የመወጣት ሚና በመሆኑ ለመምረጥ የሁላችንም ዝግጁነት ያስፈልጋል ብለዋል። የምርጫ ካርድ ከመያዝ በተጓዳኝ ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የበኩላቸውን ለመወጣት የሚሰሩ መሆኑን አስተያየት ሰጭዎቹ ገልጸዋል።
በአማራ ክልል አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት እየሰፈነ ነው-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 
Mar 25, 2026 440
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአማራ ክልል ሰላምና መረጋጋት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል ያለውን ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸው በክልሉ ሰላምና መረጋጋት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየ መሆኑን ገልፀዋል። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች፣ከከተሞች እስከ ገጠር ባደረጉት የመስክ ምልከታ የክልሉ ሰላም መሻሻል ማሳየቱን ገልጸዋል። በክልሉ ያለው ሁኔታ ቀደም ሲል በማህበራዊ ሚዲያዎች ከሚነገረው በተለየ መልኩ እጅግ የተረጋጋ መሆኑን ገልጸዋል። አሁን ያለው ችግር ከፀጥታ ስጋት ይልቅ የአስተሳሰብ ግድፈትና በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሱ መረጃዎች የፈጠሩት የስነ-ልቦና ጫና መሆኑን ጠቁመዋል። ቁጥራቸው በዛ ያሉ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ ተቀላቅለው ሰላማዊ ህይወት መጀመራቸውን ገልጸዋል። በተለይም የታጣቂ አመራር አባላት የተከናወኑ የልማት ስራዎችን እንዲጎበኙ መደረጉን አንስተዋል። በዚህም ታጣቂዎቹ የልማት ስራዎችን የመደገፍ ተነሳሽነት እንደፈጠረላቸው ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት በክልሉ እጅግ የሚያስደንቁ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተው፤ የክልሉ መንግስትና የፀጥታ ኃይሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ እየተጠናከሩ መምጣታቸውንም አክለዋል።
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ መሆን የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Mar 25, 2026 322
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ መሆን የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ዜጎች ለኢትዮጵያ ይጠቅማል የሚሉትን ለመምረጥ አስቀድመው የምርጫ ካርዳቸውን እንዲወስዱም ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፅ በሚሰጥበት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ይገኛል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በምርጫ ዝግጅት መልዕክታቸው፤ ስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሕዊና ገለልተኛ ሆኖ መጠናቀቁ የህዝብ ተቀባይነት ማስገኘቱን አስታውሰዋል። ብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ አግኝቶ በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር ለተፎካካሪ ፓርቲዎች የመንግስት ኃላፊነት በመስጠት አስቻይ የፖለቲካ ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የተፈጠረው ጤናማ የፖለቲካ ምኅዳርም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላት በሀገር ሰላም፣ ልማትና ዕድገት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። ፓርቲው ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ የሚበጁ አማራጭ ሃሳቦቻቸውን በነጻነት እንዲያቀረቡ ጽኑ ፍላጎት እንዳለው አንስተዋል። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅም መከበርን በተመለከተ የማይናወጥ አቋም ሊኖራቸው እንደሚገባም አመልክተዋል። ለዚህም የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ተሞክሮዎችን በመቀመር ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በውጤታማነት ማካሄድ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። የብልፅግና ፓርቲም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባስመዘገባቸው ተጨባጭ ውጤቶች ብቻ በህዝብ ተመራጭ መሆን የሚሻ ፓርቲ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ ፍትሐዊና መልክዓ-ምድራዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም የትውልድና የብሔራዊ ጥቅም አንጓ መሆኑን መገንዘብ እንደሚገባ አስረድተዋል። የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ የህዝብን አንድነት ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረትም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር የመስራት ባህልን ማጎልበት እንደሚኖርባቸው አንስተዋል። በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያለው መንግስት ለመመስረት የምርጫው ዴሞክራሲዊነት ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን በመገናኛ ብዙሃን ለህዝቡ እያዳረሱ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዜጎችም ድምፅ መስጫ ካርድ መውሰድ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ሰላማዊ፣ ተዓማኒና የህዝብ ተቀባይነት እንዲኖረው ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ዜጎች በጠቅላላ ምርጫው ተሳትፏቸውን በማጠናከር የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆን አለባቸው
Mar 25, 2026 336
ዲላ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ ዜጎች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተሳትፏቸውን በማጠናከር የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆናቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው ምሁራንና የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን መመዝገባቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት አማራጭ ሐሳቦች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል ከዚህ ውስጥ 2 ሺህ 198 ዕጩዎች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ 8 ሺህ 736 ለክልል ምክር ቤቶች ለመወዳደር የተመዘገቡ ሲሆን 73 የሚሆኑት ደግሞ በግል በዕጩነት የቀረቡ መሆኑን ቦርዱ አስታውቋል። በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ዲን ፍሬዘር ዓለሙ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ህዝብ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆኑ የሚረጋገጠው ያስተዳድረኛል ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ በምርጫ ካርዱ ሲሰይም ነው።   የሃሳብ ልዩነቶች የምርጫ ሂደት እድሎች በመሆናቸው ከማሸነፍና መሸነፍ በላይ የዳበረ የዴሞክራሲ ባህል በመገንባት ለቀጣይ ትውልድ ሃገርን ለማጽናት የሚቻልበት መንገድ እንደሆነ አመላክተዋል። በመሆኑም በቀጣይ አምስት ዓመት ሀገሪቱን የሚመራ ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት ዜጎች በኃላፊነት በምርጫው ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት። ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለዘላቂ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስና ስነ- ሰብ ኮሌጅ ዲን ፕሮፌሰር ዘለቀ አርፍጮ ናቸው።   የመራጮች ምዝገባ ተሳትፎ፣ የፓርቲዎች አማራጭ ፖለሲዎችን የማስተዋወቅና ክርክሮችን ማድረግ እየታየ ያለው ተሳትፎ መልካም ጅማሮ መሆኑን ጠቅሰዋል። ዜጎች በምርጫው የነቃ ተሳትፏቸውን በማጠናከር ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤት መሆናቸውን ማረጋገጥ የሚችሉበት መንገድ መሆኑንም ያስረዳሉ። በአሁኑ ወቅትም በተለይ ምሁራን የፖሊሲ አማራጮችን በመተንተንና ህዝቡ በተገቢው መንገድ ግንዛቤ እንዲይዝ በማድረግ ረገድ ሚናችንን ማጠናከር አለብን ነው ያሉት። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የአካል ጉዳተኞች ክንፍ ሰብሳቢ መአዛ ሱልጣን በበኩላቸው፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አካል ጉዳተኞች በተገቢው መንገድ ተሳትፎ እያደረግን ነው ብለዋል።   የምርጫ ስኬታማነት የጋራ ጥረት ውጤት መሆኑን አንስተው ለዚህም የመራጮች ካርድ ከመውሰድ ጀምሮ በየደረጃው የሚደረገው ተሳትፎ መጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል።
የምስራቅ እዝ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት እየተወጣ ነው -ሌተናል ጄነራል መሐመድ ተሰማ
Mar 25, 2026 233
ባህር ዳር፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ እዝ የተሰጠውን ሕገ-መንግስታዊ ተልዕኮ በላቀ ብቃትና ጀግንነት እየተወጣ እንደሚገኝ የእዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል መሐመድ ተሰማ አረጋገጡ። ሌተናል ጄነራል መሐመድ ተሰማ በቀጣናው ለተሰማሩ የዕዝ ኮማንድ፣ የኮር፣ የክፍለ ጦር እና የስታፍ መምሪያ አመራሮች የወቅታዊ ስምሪት አቅጣጫ ሰጥተዋል።   ሌተናል ጄነራሉ በዚሁ ወቅት፤ ሠራዊቱ በአገሪቱ ላይ የተደቀኑ አደጋዎችን መመከት የሚያስችል ቁመና ላይ እንደሚገኝና የአመራር አካላትም ተቀናጅተው ሚናቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። የምስራቅ እዝም አገራዊና ተቋማዊ ተልዕኮውን በጽናት በመወጣት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአማራ ክልል እየተከናወኑ በሚገኙ ህግ የማስከበር ተግባራትም የባዕዳን ተልዕኮ አስፈፃሚ የሆኑ ኃይሎች ዓላማቸው እንዲመክን መደረጉን ጠቁመዋል። በቀጣይም ከክልሉ የፀጥታ ኃይሎችና ከሕዝብ ጋር ይበልጥ በመቀናጀት በቀጣናው አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል።
የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች በምርጫው ንቁ ተሳታፊ የሚያደርጋቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ነው
Mar 25, 2026 212
ሆሳዕና፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ መሆኑን የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ በሀረሪ ክልል ወጣቶች በቅድመ ምርጫው የነቃ ተሳትፎ እያደረጉ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሔደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በዲጂታል እና በማንዋል እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የሆሳዕና ከተማ ነዋሪው ብሩክ ታደሰ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ወስደዋል፡፡   የምርጫ ካርድን በወቅቱ በመውሰድ ህገ መንግስታዊ መብትን መጠቀም እንደሚገባ በማመን የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉትን ክርክር በማድመጥና የሚያቀርቡትን ሀሳብ በመገንዘብ የሀገሪቱን ቀጣይ እጣ ፈንታ የተሻለ ማድረግ ይችላል ላሉት ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።   ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ሰናክሪም ዘውገ በበኩላቸው፤ የምርጫ ካርድ በመውሰድ የሚወክላቸውን አካል ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ነው የጠቆሙት። በምርጫው የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የሀገሪቱን እድገትና ልማት ማስቀጠል የሚችል አካልን ወደ ስልጣን ለማምጣት ማቀዳቸውንም አስታውቀዋል።   የሴቶችን መብት ከማስጠበቅና ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አኳያ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጠናከር በምርጫው የነቃ ተሳትፎ ማድረግ የሚያስችለኝን የመራጭነት ካርድ አውጥቻለው የምትለው ደግሞ ወጣት ፀጋነሽ ገብረ ሚካኤል ናት፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት አማራጭ ሐሳቦች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል
Mar 25, 2026 254
ሰመራ ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያደርጉት የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ለአገራዊ ጉዳዮች ቅድሚያ በመስጠት አማራጭ ሐሳቦች ላይ ማተኮር እንዳለባቸው በሰመራ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር አስገነዘቡ። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የሚከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል በኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን ተወስኖ፣ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ። ከቅድመ ምርጫ መርሃ ግብሮች መካከልም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ስም እንዲሁም የመለያ ምልክት አደራደር ቅደም ተከተል ለመወሰን የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት ማካሄዱ ይጠቀሳል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም የምርጫ ክርክር እና የቅስቀሳ መርሃ ግብሮቻቸውን እያካሄዱ መሆኑም ይታወቃል። በሰመራ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ካሳሁን አበራ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳመለከቱት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያደርጉት ክርክርና ቅስቀሳ አገርን ወደፊት በሚያስቀጥሉና ዘላቂ ፋይዳ ባላቸው ጉዳዮች ላይ ማተኮር ይገባቸዋል።   ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የአገርን ጥቅም ባስቀደመና ህልውናን ባስጠበቀ መልኩ የተሻሉ አማራጭ ሐሳቦችን ይዘው መቅረብ እንደሚኖርባቸውም ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ የምርጫ ሕግና ደንቦችን በአግባቡ ማክበር እንዲሁም የገቡትን ቃልና ማኒፌስቶ ተረድቶ ለሕዝብ ማሳወቅ እንደሚጠበቅባቸውም አመልክተዋል። ለመራጩ ሕዝብ ጠቃሚ ሐሳቦችን ከማቅረብ ይልቅ፣ አንዱ በሌላው ላይ ግጭት ሊቀሰቅሱ ከሚችሉ ንግግሮች መቆጠብ እንዳለባቸውም አክለዋል። በአጠቃላይ በምርጫ ሂደቱ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማጠናከር፣ የሕዝብን ድምፅና የምርጫ ውጤትን በሰላማዊ መንገድ የመቀበል ባሕል ሊዳብር እንደሚገባም አሳስበዋል።
ፖለቲካ
የምርጫ ካርድ በመውሰድ በድምፃችን የሚመራንን ፓርቲ ለመወሰን ተዘጋጅተናል
Mar 26, 2026 30
ደብረ ማርቆስ ፤መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ) ፡-የምርጫ ካርድ በመውሰድ በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የበኩላቸውን ለመወጣት የሚሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን ተወስኖ፣ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ስም እንዲሁም የመለያ ምልክት አደራደር ቅደም ተከተል ለመወሰን የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት አካሒዷል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም ፖሊሲና ስትራቴጂያቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የምርጫ ክርክርና ቅስቀሳ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም በአማራ ክልል ደብረ ማርቆስ ከተማና አካባቢው አጠቃላይ ምርጫውን በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር በየምርጫ ጣቢያዎቹ ተዘዋውሮ የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ያሉ ዜጎችን አነጋግሯል። ከየምርጫ ጣቢያዎቹ አስተያየት የሰጡ ነዋሪዎችም የምርጫ ካርድ በመውሰድ በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በከተማው ቀበሌ 11 የሚኖሩትና የምርጫ ካርድ ሲወስዱ ያገኘናቸው ወይዘሮ ውባለም ዝይን፤ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የመምረጥ እድል ያገኙ መሆኑን ተናግረው ካርድ በመውሰድ ለምርጫው ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመገናኛ ብዙሃን የሚካሄዱ የፓርቲዎችን የክርክር መድረኮች እየተከታተሉ መሆኑን አንስተው ለሀገርና ህዝብ ይበጃል ለሚሉት ፓርቲ ድምፃቸውን እንደሚሰጡም ነው የሚናገሩት። የቀበሌ 10 ነዋሪ የሆኑት አቶ አንተነህ ይርዳው፤ በአምስት አመት አንዴ የሚገኘውን እድል በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመጠቀም የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ጉዳይ የህዝብ የመወሰን መብት የሚረጋገጥበት መልካም አጋጣሚ በመሆኑ ከወዲሁ የምርጫ ካርድ በመውሰድ እድሉን መጠቀም ይገባል ብለዋል። በመሆኑም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ምርጫ ከወዲሁ ካርድ በመውሰድ በድምፃቸው የሚመራቸውን ፓርቲ ለመወሰን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ትግስት ዳኘ፤ የመራጭነት ካርዳቸውን በመያዝ ድምፃቸውን ለመስጠት ከወዲሁ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምርጫ ሂደት የዜጎች ተሳትፎ የሚረጋገጥበትና ሀገራዊ ሃላፊነትን የመወጣት ሚና በመሆኑ ለመምረጥ የሁላችንም ዝግጁነት ያስፈልጋል ብለዋል። የምርጫ ካርድ ከመያዝ በተጓዳኝ ለምርጫው ሰላማዊ ሂደት የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ የበኩላቸውን ለመወጣት የሚሰሩ መሆኑን አስተያየት ሰጭዎቹ ገልጸዋል።
በአማራ ክልል አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት እየሰፈነ ነው-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 
Mar 25, 2026 440
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአማራ ክልል ሰላምና መረጋጋት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል ያለውን ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸው በክልሉ ሰላምና መረጋጋት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየ መሆኑን ገልፀዋል። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች፣ከከተሞች እስከ ገጠር ባደረጉት የመስክ ምልከታ የክልሉ ሰላም መሻሻል ማሳየቱን ገልጸዋል። በክልሉ ያለው ሁኔታ ቀደም ሲል በማህበራዊ ሚዲያዎች ከሚነገረው በተለየ መልኩ እጅግ የተረጋጋ መሆኑን ገልጸዋል። አሁን ያለው ችግር ከፀጥታ ስጋት ይልቅ የአስተሳሰብ ግድፈትና በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሱ መረጃዎች የፈጠሩት የስነ-ልቦና ጫና መሆኑን ጠቁመዋል። ቁጥራቸው በዛ ያሉ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ ተቀላቅለው ሰላማዊ ህይወት መጀመራቸውን ገልጸዋል። በተለይም የታጣቂ አመራር አባላት የተከናወኑ የልማት ስራዎችን እንዲጎበኙ መደረጉን አንስተዋል። በዚህም ታጣቂዎቹ የልማት ስራዎችን የመደገፍ ተነሳሽነት እንደፈጠረላቸው ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት በክልሉ እጅግ የሚያስደንቁ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተው፤ የክልሉ መንግስትና የፀጥታ ኃይሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ እየተጠናከሩ መምጣታቸውንም አክለዋል።
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ መሆን የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Mar 25, 2026 322
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነጻ፣ ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ መሆን የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ዜጎች ለኢትዮጵያ ይጠቅማል የሚሉትን ለመምረጥ አስቀድመው የምርጫ ካርዳቸውን እንዲወስዱም ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፅ በሚሰጥበት የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ይገኛል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በምርጫ ዝግጅት መልዕክታቸው፤ ስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሕዊና ገለልተኛ ሆኖ መጠናቀቁ የህዝብ ተቀባይነት ማስገኘቱን አስታውሰዋል። ብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ አግኝቶ በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር ለተፎካካሪ ፓርቲዎች የመንግስት ኃላፊነት በመስጠት አስቻይ የፖለቲካ ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የተፈጠረው ጤናማ የፖለቲካ ምኅዳርም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላት በሀገር ሰላም፣ ልማትና ዕድገት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። ፓርቲው ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ የሚበጁ አማራጭ ሃሳቦቻቸውን በነጻነት እንዲያቀረቡ ጽኑ ፍላጎት እንዳለው አንስተዋል። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅም መከበርን በተመለከተ የማይናወጥ አቋም ሊኖራቸው እንደሚገባም አመልክተዋል። ለዚህም የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ተሞክሮዎችን በመቀመር ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በውጤታማነት ማካሄድ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። የብልፅግና ፓርቲም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባስመዘገባቸው ተጨባጭ ውጤቶች ብቻ በህዝብ ተመራጭ መሆን የሚሻ ፓርቲ መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ ፍትሐዊና መልክዓ-ምድራዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም የትውልድና የብሔራዊ ጥቅም አንጓ መሆኑን መገንዘብ እንደሚገባ አስረድተዋል። የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ የህዝብን አንድነት ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረትም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በትብብር የመስራት ባህልን ማጎልበት እንደሚኖርባቸው አንስተዋል። በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያለው መንግስት ለመመስረት የምርጫው ዴሞክራሲዊነት ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን በመገናኛ ብዙሃን ለህዝቡ እያዳረሱ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዜጎችም ድምፅ መስጫ ካርድ መውሰድ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም ሰላማዊ፣ ተዓማኒና የህዝብ ተቀባይነት እንዲኖረው ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ዜጎች በጠቅላላ ምርጫው ተሳትፏቸውን በማጠናከር የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆን አለባቸው
Mar 25, 2026 336
ዲላ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ ዜጎች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተሳትፏቸውን በማጠናከር የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆናቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው ምሁራንና የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች 10 ሺህ 934 ዕጩዎችን መመዝገባቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት አማራጭ ሐሳቦች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል ከዚህ ውስጥ 2 ሺህ 198 ዕጩዎች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ 8 ሺህ 736 ለክልል ምክር ቤቶች ለመወዳደር የተመዘገቡ ሲሆን 73 የሚሆኑት ደግሞ በግል በዕጩነት የቀረቡ መሆኑን ቦርዱ አስታውቋል። በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ዲን ፍሬዘር ዓለሙ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ህዝብ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆኑ የሚረጋገጠው ያስተዳድረኛል ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ በምርጫ ካርዱ ሲሰይም ነው።   የሃሳብ ልዩነቶች የምርጫ ሂደት እድሎች በመሆናቸው ከማሸነፍና መሸነፍ በላይ የዳበረ የዴሞክራሲ ባህል በመገንባት ለቀጣይ ትውልድ ሃገርን ለማጽናት የሚቻልበት መንገድ እንደሆነ አመላክተዋል። በመሆኑም በቀጣይ አምስት ዓመት ሀገሪቱን የሚመራ ፓርቲ ወደ ስልጣን ለማምጣት ዜጎች በኃላፊነት በምርጫው ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት። ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለዘላቂ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስና ስነ- ሰብ ኮሌጅ ዲን ፕሮፌሰር ዘለቀ አርፍጮ ናቸው።   የመራጮች ምዝገባ ተሳትፎ፣ የፓርቲዎች አማራጭ ፖለሲዎችን የማስተዋወቅና ክርክሮችን ማድረግ እየታየ ያለው ተሳትፎ መልካም ጅማሮ መሆኑን ጠቅሰዋል። ዜጎች በምርጫው የነቃ ተሳትፏቸውን በማጠናከር ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤት መሆናቸውን ማረጋገጥ የሚችሉበት መንገድ መሆኑንም ያስረዳሉ። በአሁኑ ወቅትም በተለይ ምሁራን የፖሊሲ አማራጮችን በመተንተንና ህዝቡ በተገቢው መንገድ ግንዛቤ እንዲይዝ በማድረግ ረገድ ሚናችንን ማጠናከር አለብን ነው ያሉት። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የአካል ጉዳተኞች ክንፍ ሰብሳቢ መአዛ ሱልጣን በበኩላቸው፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አካል ጉዳተኞች በተገቢው መንገድ ተሳትፎ እያደረግን ነው ብለዋል።   የምርጫ ስኬታማነት የጋራ ጥረት ውጤት መሆኑን አንስተው ለዚህም የመራጮች ካርድ ከመውሰድ ጀምሮ በየደረጃው የሚደረገው ተሳትፎ መጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል።
የምስራቅ እዝ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት እየተወጣ ነው -ሌተናል ጄነራል መሐመድ ተሰማ
Mar 25, 2026 233
ባህር ዳር፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ እዝ የተሰጠውን ሕገ-መንግስታዊ ተልዕኮ በላቀ ብቃትና ጀግንነት እየተወጣ እንደሚገኝ የእዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል መሐመድ ተሰማ አረጋገጡ። ሌተናል ጄነራል መሐመድ ተሰማ በቀጣናው ለተሰማሩ የዕዝ ኮማንድ፣ የኮር፣ የክፍለ ጦር እና የስታፍ መምሪያ አመራሮች የወቅታዊ ስምሪት አቅጣጫ ሰጥተዋል።   ሌተናል ጄነራሉ በዚሁ ወቅት፤ ሠራዊቱ በአገሪቱ ላይ የተደቀኑ አደጋዎችን መመከት የሚያስችል ቁመና ላይ እንደሚገኝና የአመራር አካላትም ተቀናጅተው ሚናቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል። የምስራቅ እዝም አገራዊና ተቋማዊ ተልዕኮውን በጽናት በመወጣት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል። በአማራ ክልል እየተከናወኑ በሚገኙ ህግ የማስከበር ተግባራትም የባዕዳን ተልዕኮ አስፈፃሚ የሆኑ ኃይሎች ዓላማቸው እንዲመክን መደረጉን ጠቁመዋል። በቀጣይም ከክልሉ የፀጥታ ኃይሎችና ከሕዝብ ጋር ይበልጥ በመቀናጀት በቀጣናው አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል።
የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች በምርጫው ንቁ ተሳታፊ የሚያደርጋቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ ነው
Mar 25, 2026 212
ሆሳዕና፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ እየወሰዱ መሆኑን የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ በሀረሪ ክልል ወጣቶች በቅድመ ምርጫው የነቃ ተሳትፎ እያደረጉ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሔደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በዲጂታል እና በማንዋል እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የሆሳዕና ከተማ ነዋሪው ብሩክ ታደሰ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ ወስደዋል፡፡   የምርጫ ካርድን በወቅቱ በመውሰድ ህገ መንግስታዊ መብትን መጠቀም እንደሚገባ በማመን የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉትን ክርክር በማድመጥና የሚያቀርቡትን ሀሳብ በመገንዘብ የሀገሪቱን ቀጣይ እጣ ፈንታ የተሻለ ማድረግ ይችላል ላሉት ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።   ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ሰናክሪም ዘውገ በበኩላቸው፤ የምርጫ ካርድ በመውሰድ የሚወክላቸውን አካል ለመምረጥ የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን ነው የጠቆሙት። በምርጫው የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የሀገሪቱን እድገትና ልማት ማስቀጠል የሚችል አካልን ወደ ስልጣን ለማምጣት ማቀዳቸውንም አስታውቀዋል።   የሴቶችን መብት ከማስጠበቅና ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አኳያ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጠናከር በምርጫው የነቃ ተሳትፎ ማድረግ የሚያስችለኝን የመራጭነት ካርድ አውጥቻለው የምትለው ደግሞ ወጣት ፀጋነሽ ገብረ ሚካኤል ናት፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት አማራጭ ሐሳቦች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል
Mar 25, 2026 254
ሰመራ ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያደርጉት የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ለአገራዊ ጉዳዮች ቅድሚያ በመስጠት አማራጭ ሐሳቦች ላይ ማተኮር እንዳለባቸው በሰመራ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር አስገነዘቡ። ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማነት የሚከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል በኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማካሄድ ቀን ተወስኖ፣ በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ። ከቅድመ ምርጫ መርሃ ግብሮች መካከልም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች ስም እንዲሁም የመለያ ምልክት አደራደር ቅደም ተከተል ለመወሰን የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት ማካሄዱ ይጠቀሳል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም የምርጫ ክርክር እና የቅስቀሳ መርሃ ግብሮቻቸውን እያካሄዱ መሆኑም ይታወቃል። በሰመራ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ካሳሁን አበራ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳመለከቱት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያደርጉት ክርክርና ቅስቀሳ አገርን ወደፊት በሚያስቀጥሉና ዘላቂ ፋይዳ ባላቸው ጉዳዮች ላይ ማተኮር ይገባቸዋል።   ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የአገርን ጥቅም ባስቀደመና ህልውናን ባስጠበቀ መልኩ የተሻሉ አማራጭ ሐሳቦችን ይዘው መቅረብ እንደሚኖርባቸውም ገልጸዋል። ከዚህም ባለፈ የምርጫ ሕግና ደንቦችን በአግባቡ ማክበር እንዲሁም የገቡትን ቃልና ማኒፌስቶ ተረድቶ ለሕዝብ ማሳወቅ እንደሚጠበቅባቸውም አመልክተዋል። ለመራጩ ሕዝብ ጠቃሚ ሐሳቦችን ከማቅረብ ይልቅ፣ አንዱ በሌላው ላይ ግጭት ሊቀሰቅሱ ከሚችሉ ንግግሮች መቆጠብ እንዳለባቸውም አክለዋል። በአጠቃላይ በምርጫ ሂደቱ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማጠናከር፣ የሕዝብን ድምፅና የምርጫ ውጤትን በሰላማዊ መንገድ የመቀበል ባሕል ሊዳብር እንደሚገባም አሳስበዋል።
ማህበራዊ
የአፍሪካ ወጣቶች አህጉራዊ ብልፅግናን በማረጋገጥ የራሳቸውን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መወሰን ይጠበቅባቸዋል - ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር)
Mar 25, 2026 186
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ወጣቶች አህጉራዊ ብልፅግናን በማረጋገጥ የራሳቸውን የወደፊት የተሻለ ዕጣ ፈንታ መወሰን እንደሚጠበቅባቸው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። ዩዝ ኮኔክት አፍሪካ ኢኒሼቲቭ "ከፖሊሲ ወደ ተግባር ለአፍሪካ ሰላምና መረጋጋት በአፍሪካውያን መፍትሄ ማፋጠን" በሚል መሪ ሃሳብ 6ኛውን አህጉራዊ የወጣቶች ዲፕሎማሲ ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ አካሂዷል። በኮንፍረንሱ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬን (ዶ/ር) ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት የሥራ ኃላፊዎችና የአህጉሪቱ ወጣቶች ተገኝተዋል። ሚኒስትሯ በዚሁ ወቅት፤ ዩዝ ኮኔክት አፍሪካ ኢኒሼቲቭ የአህጉሪቱን ወጣቶች የእርስ በእርስ ትስስር እያጠናከረ ነው ብለዋል። በዚህም የአፍሪካ ወጣቶች የዕውቀትና የፈጠራ ክህሎታቸውን በማሳደግ ለአህጉሪቱ ሁለንተናዊ ብልፅግና በትጋት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአህጉሪቱን መፃኢ እጣ ፈንታ ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገርም ወጣቶች የለውጥ ሞተርነታቸውን የሚያሳልጥ ዕውቀትና ክህሎት መላበስ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። 6ኛው ዩዝ ኮኔክት አፍሪካ ኢኒሼቲቭ ኮንፍረንስም የአህጉሪቱን ወጣቶች ዕውቀትና ክህሎት በማሻሻል የወጣቶች የእርስ በእርስ ትስስር በማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በአፍሪካ ወጣቶች ጥላ ስር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም የአህጉራቸውን ብልፅግና ለማረጋገጥና የራሳቸውን እጣ ፈንታ ለመወሰን ከመቸውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው መክረዋል።
ለጤናው ዘርፍ የተሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል
Mar 25, 2026 144
ሚዛን አማን፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግሥት ለጤናው ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን አመለከቱ። በክልሉ በሚዛን አማን ከተማ የአማን ጤና ጣቢያ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።   በምረቃው ወቅት አቶ ፍቅሬ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት መንግስት የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ ስራዎችን አከናውኗል። በተለይ በጤና ልማት ሥራው ከመከላከል ባሻገር አክሞ የማዳን ፖሊሲን በመከተል ጤናማና አምራች የሰው ኃይል በመፍጠር ረገድ ሰፊ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   በዚህም በክልሉ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ የተሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማድረጉን ጠቁመው፤ የጤና ተቋማት ተደራሽነትንና የአገልግሎት ጥራትን ለማስፈን እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።   የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን ህብረተሰቡ በቅርበት የጤና ተቋም አገልግሎት እንዲያገኝ የማስፋፊያ እና የአዳዲስ ጤና ተቋማት ግንባታ ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል። ከተቋም ግንባታ ባሻገር የሕክምና ግብዓት ማሟላት ሥራ ደረጃ በደረጃ እየተሠራ ሲሆን የመድኃኒት እጥረት እንዳይከሰት በሁሉም መዋቅሮች የማህበረሰብ መድኃኒት ቤቶችን የማቋቋም ተግባር መከናወኑን ጠቅሰዋል።   መንግሥት ለችግሮች መፍትሔ የመስጠት ባህሉን በቅርብ ዓመታት ጊዜ ውስጥ በማዳበሩ ለዘመናት ጥያቄ ሆነው የቆዩ የአማን ጤና ጣቢያን ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶች እየተመረቁ ነው ብለዋል። ዛሬ የተመረቀውን የአማን ጤና ጣቢያ ደረጃን ከፍ ለማድረግ በቀጣይ የተለያዩ የማስፋፊያ ሥራዎች እንደሚተገበሩ አመልክተዋል። የጤና ጣቢያው መመረቅ በከተማዋ ውስጥ የሚታየውን የሕክምና ተቋማት ጫና ይቀርፋል ያሉት ደግሞ የሚዛን አማን ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ሌዊ ናቸው።   ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ፕሮጀክቶችን የመገንባት ሥራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል። የአማን ጤና ጣቢያ መመረቅ በቅርበት የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እንደሚያስችላቸው የገለጹት ደግሞ ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ግራዎ የኪ እና ሀብታሙ ሀይጢ ናቸው።   የጤና ጣቢያ ግንባታን ለረጅም ዓመታት መጠየቃቸውን ገልጸው አሁን ላይ መንግሥት ምላሽ በመስጠቱ መጉላላትን ይቀርፋል ብለዋል። የአማን ጤና ጣቢያ በከተማዋ ከሚገኙ ጤና ጣቢያዎች ሦስተኛው ሲሆን በሚዛን አማን እና ዙሪያው ላሉ የከተማዋ ነዋሪዎች አገልግሎት የሚሰጥ ነው። ከጤና ጣቢያው ምረቃ ባሻገር ከ67 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነቡ ሦስት ድልድዮችና አንድ የግብይት ማዕከል የመሠረት ድንጋይ በዛሬው ዕለት መቀመጡም ተመልክቷል።    
ኢመደአ በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
Mar 25, 2026 106
አርባምንጭ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር(ኢመደአ) በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ። በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ተፈናቅለው በጊዜያዊ መጠለያ ለሚገኙ ወገኖች ከተለያዩ አካላት እየተደረገ ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በድጋፉም መንግስታዊ፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ ግለሰቦችና ሌሎችም በመሳተፍ ለተጎጂዎች አጋርነታቸውን እያሳዩ ይገኛሉ። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርም በዛሬው ዕለት የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።   የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ትዕግስት ሃሚድ እንደገለጹት በጋሞ ዞን በተከሰተው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት በወገኖቻችን ላይ በደረሰው አደጋ እጅግ ማዘናቸውን ገልጸዋል። ተቋሙ አደጋው ከተከሰተ ወዲህ ለጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጃ የሚያገለግል ድሮንና ባለሙያዎችን በመላክ የአየር ላይ ካርታ በማንሳት የበኩሉን ሲያከናውን መቆየቱን አውስተዋል። በዛሬው ዕለት ደግሞ ሁለት ሚሊዮን ብር የገንዘብና እና ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የተለያዩ መድኃኒቶችን፣ አልባሳትና ምግብ ነክ ቁሳቁስ ለጋሞ ዞን አስተዳደር ማስረከባቸውን ጠቁመዋል፡፡ የተፈናቀሉ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ተግባር የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ እንደሚቀጥልም ዋና ዳይሬክተሯ አረጋግጠዋል፡፡   የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ለተጎጂዎች ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። ዞኑ ለተፈናቃዮች አስፈላጊ ስፍራ ማዘጋጀቱን ጠቅሰው ተፈናቃዮችን መልሶ ለማቋቋም ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ ተግባር እያከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል።
በክልሉ የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል
Mar 25, 2026 156
ቦንጋ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በትራፊክ አደጋ ምክንያት የሚጠፋውን የሰው ሕይወትና የሚወድመውን ንብረት ለመታደግ ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረው እንደቀጠሉ የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው ከመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ጋር በመተባበር ለአሽከርካሪዎች፣ ለመናሐሪያ የስምሪት ኃላፊዎችና ለአመራሮች የአሰልጣኞች ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።   የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዘመዴ አንዳርጌ እንደገለጹት፤ የትራንስፖርት ዘርፉ ውጤታማና ጤናማ እንዲሆን የአሽከርካሪዎችንና የዘርፉ ተዋናዮችን አቅም በሥልጠና ማብቃት ወሳኝ ነው። እስካሁንም በክልሉ 15 ሺህ አሽከርካሪዎች ሥልጠና መውሰዳቸውንና በትምህርት ቤቶችና በሃይማኖት ተቋማት ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። ዘርፉን ለማዘመን 250 ሚሊዮን ብር በጀት ተመድቦ ዘመናዊ የመናሐሪያ ግንባታዎች፣ የተሽከርካሪዎች ብቃት ምዘና ማዕከል እና በአሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማት የጥራት ማሻሻያ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።   በቀጣይም በትራፊክ አደጋ የሚጠፋውን የሰው ሕይወትና ንብረት ለመታደግ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ቅንጅታዊ ስራ ይጠናከራል ብለዋል። የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፤ የትራንስፖርት ዘርፉ ለብዙዎች የሥራ ዕድል የሚፈጥርና የሕዝቦችን እንቅስቃሴ የሚያሳልጥ መሆኑን አስታውሰዋል።   አገልግሎቱን ለማዘመንና ደህንነቱን ለመጠበቅ ኃላፊነት መወጣት ከሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የፌዴራል የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሐመድ ሀሰን፤ ባለፉት አራት ዓመታት በዘርፉ ውጤቶች ቢመዘገቡም፣ ካለው ችግር አንጻር አሁንም ገና ብዙ ሥራ እንደሚቀር ተናግረዋል።   የሙያ ብቃት ማሳደጊያ ስልጠና የወሰዱ አሽከርካሪዎች የተሰጣቸውን ሥልጠና ወደ ተግባር በመቀየር እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለመቀነስ መትጋት አለባቸው ብለዋል። በመድረኩ የክልልና የፌዴራል አመራሮች፣ ባለሙያዎች፣ አሽከርካሪዎችና የመናሐሪያ የስምሪት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
በምስራቅ ጎጃም ዞን በመስኖ ከለማው መሬት እሰካሁን ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል
Mar 26, 2026 18
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን በያዝነው በጋ በአንደኛው ዙር በመስኖ ከለማው መሬት ላይ እስካሁን ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ኃላፊ አቶ አበበ መኮንን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከለውጡ ወዲህ በምግብ ራስን ለመቻል የመስኖ ልማት አንዱ አማራጭ ተደርጎ እየተሰራ ይገኛል። በበጀት ዓመቱም በአንደኛው ዙር ከ41 ሺህ 300 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ሰብል በመሸፈን ከ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አውስተዋል። ከ125 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከለማው 41 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እስካሁን ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል። የተጠቀሰውን ያህል ምርት መሰብሰብ የተቻለውም ቀድመው ከደረሱ ገብስና የተለያዩ የጓሮ አትክልቶች መሆኑን ጠቁመው ቀሪውን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የመስኖ ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግም ከ84 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘርና ከ9 ሺህ 700 በላይ የውሃ መሳቢያ ፓምፖች ጥቅም ላይ መዋላቸውን አስረድተዋል። በዞኑ የአዋበል ወረዳ የሰንበት ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጌታሁን ይርሴ እንደገለጹት በመስኖ ልማት በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ በማምረት ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት በመስኖ ካለሙት መሬት 10 ኩንታል ስንዴና 20 ኩንታል የጓሮ አትክልት ማግኘታቸውን አውስተው ዘንድሮ ከዚህ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል። በዚሁ ወረዳ የወጀል ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ይከበር ነጋ በበኩላቸው በያዝነው በጋ ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን በመስኖ ልማት መሸፈናቸውን አስረድተዋል። በየዓመቱ ከመስኖ ልማት የሚገኘውን ምርት በመሸጥ ከ60 ሺህ ብር በላይ ገቢ እንደሚያገኙ አውስተው ዘንድሮም ከዚህ የበለጠ ገቢ እንደሚያገኙ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።    
አገልግሎቱ 500 ሺህ ስማርት የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን የመግጠም ሥራ እያከናወነ ነው
Mar 26, 2026 68
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ 500 ሺህ ስማርት የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን ለነባርና አዲስ ደንበኞቹ የመግጠም ሥራ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር ለኢዜአ እንዳሉት፤ በፕሮጀክቱ 125 ሺህ ስማርት ሶስት ፌዝ፣ 25 ሺህ ስማርት ነጠላ ፌዝ እንዲሁም 350 ሺህ ኦፍላይን (Semi-Smart) ነጠላ ፌዝ ዘመናዊ የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን የመግጠም ሥራ እየተከናወነ ነው። እስካሁን በተከናወነው ሥራ 60 ሺህ 457 ነጠላ ፌዝ ቆጣሪዎችን እስከ 7 ነጥብ 5 ኪሎ ዋት ድረስ ኃይል ለሚጠቀሙ ለመኖሪያና ለንግድ ደንበኞች መገጠማቸውን አስረድተዋል። በተጨማሪም 7 ሺህ 13 ባለ ሦስት ፌዝ ቆጣሪዎች ከ8 እስከ 24 ኪሎ ዋት ድረስ ኃይል ለሚጠቀሙ ለመኖሪያ፣ ለንግድና ለአነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ተገጥመው አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህ ዘመናዊ ቆጣሪዎች የቅድመ ክፍያ ደንበኞች ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ሳይሄዱ የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ቶክን ቁጥር በመግዛት የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲሞሉ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል፡፡   ስማርት የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን ለነባርና አዲስ ደንበኞች የመግጠም ሥራው እየተከናወነ የሚገኘው በ48 ነጥብ 8 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ መሆኑንም አስታውቀዋል። ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ከ67 ሺህ በላይ ደንበኞች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በኢትዮ ቴሌኮምና በአዋሽ ባንክ የሞባይል አፕሊኬሽኖች በሳምንት ሰባቱንም ቀናት 24 ሰዓት የትም መሄድ ሳይጠበቅባቸው ቤታቸው ሆነው የኤሌክትሪክ ኃይል መግዛት እንዲችሉ ዕድል ፈጥሯል ነው ያሉት፡፡ ይህ ፕሮጀክት ቀደም ሲል የነበሩ የቅድመ ክፍያ ካርድ መጥፋት፣ የካርድ መበላሸት፣ የኔትዎርክ መቆራረጥ እንዲሁም ቆጣሪው ላይ ብር አልገባልኝም የሚሉትን ችግሮች ይቀርፋል ሲሉም አረጋግጠዋል። በተጨማሪም ከፍተኛ በሆነ ኃይል መጨመር (Over voltage) ምክንያት የሚመጣን የንብረት አደጋ ይከላከላል፣ ደንበኞች በሚሰጣቸው መሳሪያ አማካኝነት ፍጆታቸውን መከታተል በመቻላቸው አጠቃቀማቸውን መቆጠብ እና ወጪ እንዲቀንሱ ያስችላቸዋል ነው ያሉት፡፡  
በአዲስ አበባ ሕገ ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመግታት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Mar 25, 2026 278
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ሕገ ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመግታት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕግ ማስከበርና ቁጥጥር ንዑስ ኮሚቴ ባለፉት አራት ወራት ከአስራ አምስት ቀናት የሕግ ማስከበር እና የቁጥጥር ሥራዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል።   በውይይቱ ነዳጅን ጨምሮ በመዲናዋ የሸቀጦች ግብይትን ያለደረሰኝ የሚፈጽሙ ህገ ወጥ ነጋዴዎችና ሕገ ወጥ የደላላ እንቅስቃሴዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ የቀጣይ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊና የሕግ ማስከበርና ቁጥጥር ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሊዲያ ግርማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በመዲናዋ የሕገ ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመግታት የተሰሩ ሥራዎች ውጤት እያመጡ ነው። እንዲያም ሆኖ አሁንም ነዳጅን በጄሪካን ጨምሮ በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰቦች እጅ መኖሩን መለየቱን ገልጸው፤ ሕገ ወጥ የነዳጅ ዝውውር ላይ የሚደረገው ቁጥጥር ይበልጥ ይጠናከራል ብለዋል። ሰላምና ጸጥታ፣ ደንብ ማስከበር፣ የአዲስ አበባ ፖሊስና የንግድ ቢሮ ቅንጅታዊ አካሄድ ከበፊቱ በላቀ መልኩ ሊተገበር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። የቁጥጥር ሥራው በዘመናዊ መልኩ እንዲካሄድ ትኩረት መስጠት እንደሚገባም አመልክተዋል። የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ ተስፋዬ ደንድር በበኩላቸው፤ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተደረገ ቁጥጥርና ክትትል 50 ሺህ 942 ሊትር ናፍጣ በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር መያዙን ገልጸዋል። በተመሳሳይም 8 ሺህ 974 ሊትር ቤንዚን በቁጥጥር ሥር ውሏል ያሉት ኃላፊው፤ 35 ግለሰቦችም በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉን ተናግረዋል። ተሽከርካሪዎች ላይ ተጨማሪ ሳልቫቲዮ በመግጠም በሕገ ወጥ መንገድ ነዳጅ ማዘዋወር፣ የነዳጅ ማደያዎች አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች እንዲሁም የቁጥጥር ሥራው ወጥ አለመሆን በውስንነት ከሚጠቀሱ ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል እንደሚገኙበት አብራርተዋል።   የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደገለጹት፤ በአዲስ አበባ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት የለም። እጥረቱ ሰው ሰራሽ ነው ያሉት ኃላፊዋ፤ በምሽት የሚሸጥ ነዳጅ ላይ የተቀናጀና ጠንካራ የቁጥጥር ሥራ ይጠይቃል ብለዋል። የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮም በሕገ ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ ነዳጅ አቅራቢዎች ወደ ሕጋዊ መስመር እንዲገቡ የማወያየት ሥራዎች በሰፊው እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ጠቅላይ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድ እንደተናገሩት፤ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴን ለመግታት ዘላቂው መንገድ በሕገ ወጥ ተግባር ላይ የሚሰማሩትን ግንዛቤ በማስጨበጥ መመለስ ነው።   ሕግን አለመዋቅ ከተጠያቂነት አያድንም ያሉት ምክትል ኮሚሽነሩ፤ በሕገ ወጥ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ወደ ሕጋዊ መስመር ሊገቡ እንደሚገባም አሳስበዋል። የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጥበቡ ደጀኔ (ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፤ ተጨማሪ ሳልቫቲዮ የተገጠመላቸው ተሽከርካሪዎች በሕገ ወጥ መንገድ ነዳጅ እንደሚያዘዋውሩ በቁጥጥርና ክትትል ተለይቷል። ቁጥጥሩ ከነዳጅ ማደያዎች ባለፈ ተሽከርካሪዎች ላይ ሊደረግ እንደሚገባ ገልጸው፤ መንደሮች ውስጥም ጭምር በተጠናከረ መልኩ ሊካሄድ ይገባል ብለዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ምክትል መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ዳንኤል ጥላሁን እንደገለጹት፤ በክፍለ ከተማው ነዳጅ ማደያዎች በአግባቡ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ክትትል እየተደረገ ነው።
የአዲስ አበባ ፈጣን የልማት ዕድገት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ የማስረከብ ትልም ፍሬ እያፈራ መሆኑን የሚያሳይ ነው
Mar 25, 2026 200
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስደናቂ የልማት ዕድገት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ የማስረከብ ትልም ፍሬ እያፈራ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም በአዲስ አበባ ተካሂዷል።   በመርሃ ግብሩ ላይ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጣሊያን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ምክትል ሚኒስትር ማሪያ ትሪፖዲ፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ እና ተጋባዦች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመዲናዋ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ የልማት ስኬቶች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻነትን እያሳደገ ነው። የዓለም ሶስተኛዋ የዲፕሎማሲ ማዕከል የአፍሪካ መዲናና ውቧ አዲስ አበባ የአህጉሪቷ የመግቢያ በርነትን በፍጥነት እያሳደገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የአዲስ አበባን ምቹና ተወዳዳሪነት ለማሳለጥ በተገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ውስጥ የነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ቅድሚያ እንደተሰጠው አስረድተዋል። በመዲናዋ በመሠረተ ልማት መስክ የተመዘገቡ ውጤቶችም የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ትልም ፍሬ እያፈራ መሆኑን ያሳያል ብለዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የአገልግሎት አሰጣጠን ለማሳለጥ የተወሰዱ ርምጃዎች ኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት የስበት ማዕከል እያደረጋት እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡ የአዲስ አበባ የአዲስ መሶብ የዲጂታል የአንድ ማዕከል ለአልሚ ባለሃብቶች የተሳለጠ የመንግስት አገልግሎት የሚያገኙበትን አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩንም ገልጸዋል። የአዲስ አበባን ፈጣን ዕድገት በማሳለጥ ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢን በመፍጠር የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ እያበረታታ መሆኑን አንስተዋል። የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም የመዲናዋን የኢንቨስትመንት አማራጮች ለማሳየት ገንቢ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያና ጣሊያን ወዳጅነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳጅነትም የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብርን በማጠናከር ከፍተኛ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ አንስተዋል። በንግድና ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚ ባለሃብቶች ድጋፍና ትብብር እንደሚደረግ ጠቅሰው፤ የጣሊያን ባለሃብቶች ዕድሉን እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የመንግስት አገልግሎቶችን ፈጣን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ ለማድረግ እያገዘ ነው
Mar 25, 2026 73
ባህር ዳር፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የመንግስት አገልግሎቶችን ፈጣን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ለመስጠት እያስቻለ መሆኑን የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። ዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በብሔራዊ ደረጃ የሚያገኙበት ሕጋዊና መሠረታዊ የመታወቂያ ዓይነት መሆኑም ይታወቃል። የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ የቻለ ይግዛው ለኢዜአ እንዳሉት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች በየደረጃው ፈጣንና ፍትኃዊ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ እያስቻለ ነው ። በተለይም መታወቂያውን ከባንክና ሌሎች አሰራሮች ጋር በማስተሳሰር ወጥ የሆኑ አገልግሎቶችን በፍጥነትና በፍትሃዊነት ለማቅረብ እያገዘ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በክልሉ ቀልጣፋ አገልግሎቶችን ለመስጠት ከማስቻሉ ባሻገር ህገ- ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የራሱ ድርሻ እንዳለውም ጠቅሰዋል። በተያዘው ዓመትም ከ4 ሚሊዮን የሚልቁ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ መቻሉንም ነው ያመለከቱት። ፋይዳ የዜጎች ትክክለኛ ማንነት የሚገልፅ መሆኑን አመልክተው ደሕንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ከጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቀላጠፈ አገልግሎት አግኝተናል
Mar 25, 2026 70
ጅማ፤መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፡- የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተቀላጠፈ አገልግሎት ከመስጠቱ ባለፈ ለአቅመ ደካሞችም እፎይታን መስጠቱን ነዋሪዎች ገለፁ፡፡ ማዕከሉ ስራ ከጀመረ ስድስት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ነዋሪዎች ሁሉንም አገልግሎት በአንድ ማዕከል በማግኘታቸው ጊዜና ገንዘባቸውን መቆጠብ ችለዋል። ኢዜአ ካነጋገራቸው የከተማው ተገልጋዮች መካከል አቶ ኑሪ የሱፍ፤ የውኃ እና የመብራት ክፍያዎችን ለመክፈል ከዚህ ቀደም ቀናትን ይወስድባቸው እንደነበር አስታውሰዋል። እሁን ላይ ግን በከተማው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚፈልጉትን ክፍያ በአጭር ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። ለነዚህ አገልግሎቶች ሲያወጡ የነበሩትን የትራንስፖርት እና ተጨማሪ ወጪዎች ማስቀረታቸውንም ይገልጻሉ። ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ሙክታር ኢብራሂም ከመሬት ይዞታ ጋር የተያያዘ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ማዕከሉ መምጣታቸውን ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም ለመሰል አገልግሎት ወደተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች በየቀኑ ይመላለሱ እንደነበር ተናግረው አሁን በግማሽ ቀን ውስጥ ተጠናቆልኛል ብለዋል።   የጅማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት ከ84 ሺህ በላይ አገልግሎቶችን መስጠቱን የተናገሩት ደግሞ የማዕከሉ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዲ ሰለሞን ናቸው። ወደ ማዕከሉ 25 ሴክተሮች የገቡ ሲሆን በሴክተሮቹ 135 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ጠቅሰው 103 ሠራተኞች ለማኅበረሰቡ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አንስተዋል። ከዚህ በተጨማሪም አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞችን ያማከለ ምቹ አገልግሎትም እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። አገልግሎት ሰጪ ሠራተኞች ወደ አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞች ቀርበው ከማገልገል በተጨማሪ ልዩ የሊፍት አገልግሎት መዘጋጀቱንም ገልጸዋል። በቀጣይ በከተማዋ በሚገኙ ቀበሌዎች ቅርንጫፎችን በመክፈት ይበልጥ ወደ ማኅበረሰቡ ለመቅረብ ታቅዷል ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም የማዕከሉን አገልግሎት ተንቀሳቃሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን አቶ አብዲ ተናግረዋል።
የ'አዲስ መሶብ' የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተደራሽ ይሆናል
Mar 24, 2026 250
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የ'አዲስ መሶብ' የአንድ ማዕከል አገልግሎት እስከ ሚያዚያ 2018 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተደራሽ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የ'አዲስ መሶብ' የአንድ ማዕከል የተገልጋዮችን እንግልት በማስቀረት ውጤታማነትን እያረጋገጠ ነው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ'አዲስ መሶብ' ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የልደታ ቅርንጫፍን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።   ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፈጣን የህዝብ አገልግሎት በዜጎች እና በመንግሥት መካከል ያለውን መተማመን ያጎለብታል፡፡ በመሆኑም መንግሥት ዘርፉን ለማዘመንና ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ ስልቶችን በመንደፍ በርካታ ጥረቶችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ ከነዚህ ጥረቶችና ተነሳሽነቶች መካከል የአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንዱ መሆኑን አውስተዋል፡፡ በዚህም በርካታ ብልሹ አሰራሮችንና አላስፈላጊ የደንበኛ ምልልሶችን በማስቀረት ስር-ነቀል ለውጥ ማምጣት መቻሉን አመላክተዋል፡፡   ከዚህ ቀደም ተገንብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የ'አዲስ መሶብ' የአንድ ማዕከላት የህዝቦችን የጊዜ እና የገንዘብ ብክነት ትርጉም ባለው መልኩ እንዳስቀሩ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በፊት በተገነቡ የ'አዲስ መሶብ' ዲጂታል የአንድ ማዕከላት ከ120 ሺህ በላይ ዜጎችን ተደራሽ ማድረግ እንደተቻለ አመላክተዋል፡፡ እነዚህ ደንበኞች በሰጡት አስተያየት መሰረት የደንበኞች እርካታ 98 በመቶ መድረስ መቻሉ ተረጋግጧል ነው ያሉት፡፡ በተያዘው ወር ብቻ ተጨማሪ ሶስት የ'አዲስ መሶብ' የአንድ ማዕከላት ለመገንባት ታስቦ ወደ ተግባር መገባቱን ያመላከቱት ከንቲባዋ፤ እስከ ሚያዚያ ወር መጨረሻ ድረስም የከተማዋ ሁሉም ክፍለ ከተሞች በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽ እንደሚሆኑ ገልጸዋል፡፡   በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀምበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የ'አዲስ መሶብ' የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ አንድ አሰባስቧል ብለዋል፡፡ በ18 ተቋማት እና በ107 አገልግሎቶች ስራ የጀመረው የ'አዲስ መሶብ' የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን ላይ የተቋማትን ቁጥር ወደ 22 እና የአገልግሎቶችን ቁጥር ደግሞ ወደ 140 ከፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ በዛሬው ዕለት ለምረቃ የበቃው ማዕከል የክፍለ ከተማችንን አገልግሎት አሰጣጥ እርስ በእርስ የሚያስተሳስር ነው ያሉት ደግሞ የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ልዕልቲ ግደይ ናቸው፡፡
የኮደርስ ስልጠና መውሰዳችን ተጨማሪ እውቀትና ክህሎት ከማግኘት ባለፈ በዘርፉ ብቁ ተወዳዳሪ መሆን አስችሎናል
Mar 24, 2026 109
መቀሌ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦ የኮደርስ ስልጠና መውሰዳችን ተጨማሪ እውቀትና ክህሎት ከማግኘት ባለፈ በዘርፉ ብቁ ተወዳዳሪ እንድንሆን አስችሎናል ሲሉ በመቀሌ ከተማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ ወጣቶች ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተመቻቸው የአምስት ሚሊየን የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና በተለይም ወጣቶች የእድሉ ተጠቃሚ ሆነው ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑ ይታወቃል። የስልጠናው ዓላማ በዘርፉ የዜጎችን አቅም ከመገንባት ባለፈ ኢትዮጵያ በዘርፉ ልማት የጀመረችው እድገትና ማንሰራራት ቀጣይነት እንዲኖረው የሚያደርግም ነው። በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ዜጎች ስልጠናውን እየወሰዱ ከራሳቸው አልፈው ለሀገራቸው የዲጂታል ልማት ስትራቴጂ ትግበራ አሻራቸውን እያኖሩ መሆኑ ይታወቃል። በዚሁ መሰረት በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ስልጠናውን የወሰዱ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና በመውሰዳችን ተጨማሪ እውቀትና ክህሎት ከማግኘት ባለፈ በዘርፉ ብቁ ተወዳዳሪ መሆን አስችሎናል ብለዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡ ወጣቶች መካከል ወጣት አኸዛ ወልደጊወርጊስ፤ የኮደርስ ስልጠና በመውሰድ በዘርፉ የተሻለ ክህሎትና እውቀት ያገኘችበት መልካም እድል መሆኑን ገልፃለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁ ተወዳዳሪ በመሆን ከራስ ተጠቃሚነት አልፎ በዲጂታል የአገልገሎት ዘርፍ ጥራትና ፍጥነት ያለው አገልግሎት ለመስጠትም ወሳኝ መሆኑን ተናግራለች። ስልጠናውን ከወሰዱ ወጣቶች መካከል ሰሎሞን ገብረመድህን እና ጸጋአብ ገብረእግዛብሄር፤ የኮደርስ ስልጠናው በተለይም ለወጣቶች መልካም እድል ይዞ የመጣ መሆኑን ተናግረዋል። ስልጠናውን በመውሰዳቸው በዘርፉ ብቁ ተወዳዳሪ እና የስራ እድል ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን በተግባር አይተነዋል ያሉት ወጣቶቹ ሌሎችም ጊዜ ሳያባክኑ እድሉን እንዲጠቀሙበት መክረዋል። የኮደርስ ስልጠናው የዳታ ሳይንስ፣ ዌብ ፕሮግራሚንግ፣ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስና አንድሮይድ የማበልጸግ እና ሌሎች ተያያዥ ዕውቀቶችን ማግኘት የሚያስችል መሆኑ ይታወቃል።
ስፖርት
ወደ ዓለም ዋንጫ የሚያልፉ ቀሪ ስድስት ሀገራት የሚለዩባቸው የማጣሪያ ጨዋታዎች 
Mar 26, 2026 74
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ 23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ ጣምራ አዘጋጅነት ከሰኔ 4 እስከ ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። በዓለም ዋንጫው 48 ሀገራት የሚሳተፉ ሲሆን፤ እስከ አሁን 42 ሀገራት የተሳትፎ ትኬታቸውን ቆርጠዋል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ቀሪ ስድስት ሀገራት የሚለዩባቸው የመጀመሪያ ዙር የማጣሪያ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ።   የዓለም ዋንጫ የአውሮፓ ጥሎ ማለፍ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ይከናወናሉ። ምሽት 2 ሰዓት ላይ ቱርክዬ ከሮማንያ በቱፕራስ ስታዲየም ይጫወታሉ። የአራት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ጣልያን ከሰሜን አየርላንድ፣ ዴንማርክ ከሰሜን ሜቄዶኒያ፣ ፖላንድ ከአልባኒያ፣ ቼክ ሪፐብሊክ ከአየርላንድ፣ ዩክሬን ከስዊድን፣ ስሎቫኪያ ከኮሶቮ እና ዌልስ ከቦሲኒያ እና ሄርዞጌቪና በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ከ45 ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፉ ሀገራት ለዓለም ዋንጫው ለማለፍ ወደሚደረገው የመጨረሻ ማጣሪያ ያልፋሉ። በመጨረሻው ማጣሪያ የጣልያን እና ሰሜን አየርላንድ አሸናፊ ከዌልስ እና ቦሲኒያና ሄርዜጎቪና አሸናፊ፣ የፖላንድ እና አልባኒያ አሸናፊ ከዩክሬንና ስዊድን አሸናፊ፣ የቱርክዬና ሮማኒያ አሸናፊ ከስሎቫኪያና ኮሶቮ አሸናፊ እንዲሁም የዴንማርክ እና ሰሜን ሜቄዶኒያ አሸናፊ ከቼክ ሪፐብሊክ እና አየርላንድ አሸናፊ ጋር ይጫወታሉ። የመጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጨዋታዎችን የሚያሸንፉ አራት ሀገራት ለዓለም ዋንጫ ማለፋቸውን ያረጋግጣሉ። አራቱ ሀገራት አስቀድመው በቀጥታ ወደ ዓለም ዋንጫ ያለፉ 12 የአውሮፓ ሀገራትን ይቀላቀላሉ። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከአውሮፓ 16 ሀገራት ይሳተፋሉ። በተያያዘም የክፍለ አህጉራት የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ ጨዋታዎችም ይካሄዳሉ። በማጣሪያው ላይ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (አፍሪካ)፣ ኢራቅ (እስያ)፣ ቦሊቪያ (ደቡብ አሜሪካ)፣ ሱሪናም (ሰሜን/ማዕከላዊ አሜሪካ እና ካሪቢያን)፣ ጃማካይ (ሰሜን/ማዕከላዊ አሜሪካ እና ካሪቢያን) እና ኒው ካሌዶኒያ (ኦሽንያ) ይሳተፋሉ። በፊፋ የሀገራት የእግር ኳስ ደረጃ የተሻለ ደረጃ ያላቸው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (48ኛ) እና ኢራቅ (55ኛ) በቀጥታ ወደ መጨረሻው የማጣሪያ ጨዋታ አልፈዋል። ቀሪዎቹ አራት ሀገራት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታቸውን በሜክሲኮ ያደርጋሉ። ቦሊቪያ ከሱሪናም ከሌሊቱ 7 ሰዓት በስታዲዩ ቢቢቪኤ፣ ኒው ካሌዶኒያ ከጃማይካ በአክሮን ስታዲየም ከጠዋቱ 12 ላይ ይጫወታሉ። የኒው ካሌዶኒያ እና ጃማይካ አሸናፊ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ የቦሊቪያ እና ሱሪናም አሸናፊ ከኢራቅ ጋር ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታቸውን ያሸነፉ ሁለት ሀገራት ለዓለም ዋንጫው ያልፋሉ።
የመውረድ ስጋት ያለባቸው ክለቦች የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ 
Mar 26, 2026 66
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ዛሬ ይጠናቀቃል። ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ ይርጋጨፌ ቡና ከአዲስ አበባ ከተማ በአበባ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ይርጋጨፌ ቡና በሊጉ ባደረጋቸው 20 ጨዋታዎች በሁለቱ አሸንፎ በ13ቱ ተሸንፎ በአምስቱ አቻ ወጥቷል። በ20ዎቹ ጨዋታዎች ዘጠኝ ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 31 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አዲስ አዳጊው ይርጋጨፌ ቡና በ11 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው አዲስ አበባ ከተማ በሊጉ 20 ጨዋታዎች አከናውኖ ሶስት ጊዜ ድል ሲቀናው፤ በ15ቱ ተሸንፏል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። 12 ግቦችን ሲያስቆጥር 41 ጎሎችን አስተናግዷል። አዲስ አበባ ከተማ በተመሳሳይ 11 ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ 13ኛ ደረጃን በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ይርጋጨፌ ቡና ባለፉት 12 የሊግ ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ያስገኝለታል። በአንጻሩ አዲስ አበባ ከተማ ካሸነፈ ከወራጅ ቀጠና ይወጣል።   በሌላኛው መርሐ-ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከአርባምንጭ ከተማ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ድሬዳዋ ከተማ እስከ አሁን በሊጉ ማሸነፍ የቻለው ጨዋታ ብዛት ስድስት ነው። 11 ጊዜ ሲሸነፍ ሶስት ጊዜ አቻ ወጥቷል። 18 ግቦችን ሲያስቆጥር 31 ጎሎችን አስተናግዷል። ቡድኑ በ21 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ተጋጣሚው አርባምንጭ ከተማ በበኩሉ 20 ጨዋታዎችን አድርጎ ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ፤ 14 ጊዜ ተሸንፏል። በአራት ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 10 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 37 ጎሎች ተቆጥረውበታል። አርባምንጭ ከተማ በ10 ነጥብ የመጨረሻውን 14ኛ ደረጃን ይዟል። ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት አምስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። አርባምንጭ ከተማ ባለፉት 13 ጨዋታዎች ከድል ርቋል። ሁለቱም ቡድኖች ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። ጨዋታዎቹ ላለመውረድ በሚደረገው ፉክክር ወሳኝ የሚባሉ ናቸው።   ቦሌ ክፍለ ከተማ ከባህር ዳር ከተማ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ። ቦሌ ክፍለ ከተማ በ31 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ባህር ዳር ከተማ በ16 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ባለፉት አራት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ከድል የራቀው ቦሌ ክፍለ ከተማ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ባህር ዳር ከተማ ካሸነፈ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ያስመዘግባል።
አዲስ አበባን ጽዱ፣ ውብና አረንጓዴ በማድረግ ለወጣቶች ምቹ የልማት ማዕከል የመገንባት ራዕይ በተግባር እየተረጋገጠ ነው
Mar 25, 2026 69
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባን ጽዱ፣ ውብና አረንጓዴ በማድረግ ለወጣቶች ምቹ የመዝናኛና የልማት ማዕከል የመገንባት ሥራ በተግባር እየተረጋገጠ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰግደው ኃይለጊዮርጊስ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በአራዳ ፓርክ የወጣቶች የኪነ-ጥበብ እና የፈጠራ ስራዎች የቀረቡበት መርሀ-ግብር አካሂዷል፡፡   የቢሮው ኃላፊ አቶ አሰግደው ኃይለጊዮርጊስ በዚሁ ወቅት፤ ከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችን ታሳቢ ያደረጉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ማቀድ ብቻ ሳይሆን በተግባር በመፈጸም ውጤታማነቱን እያሳየ ይገኛል። በወንዝ ዳርቻና በኮሪደር ልማት የተገነቡ የወጣት ማዕከላት የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና በመጫወት ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ በአራዳ ፓርክ የተካሄደው ወጣቶች የተሳተፉበት የባህላዊ ውዝዋዜ፣ የኪነ ጥበብ እና የፈጠራ ስራዎች መርሃ-ግብር ለዚህ ስኬት አብነት መሆኑን ጠቅሰዋል። እነዚህ ስፍራዎች ወጣቶች አብሮነታቸውንና ወንድማማችነታቸውን የሚያጠናክሩባቸው የጋራ መድረኮች ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉም ብለዋል። መሰል የማዘውተሪያ ስፍራዎች ወጣቶች በሀገራቸው ላይ ትልቅ ተስፋ እንዲሰንቁና የፈጠራ አቅማቸውን ወደ ላቀ ደረጃ እንዲያሸጋግሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ አስረድተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ደጋፊዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ምንያህል ጌታቸው እንዳለውም፣ አዲስ አበባ እንደ ስሟ እያበበች መሆኗን ገልጿል። የተገነቡት ማራኪ የመዝናኛ ስፍራዎች መንግስት ለወጣቱ ትውልድ የሚሰጠውን ልዩ ትኩረት የሚያሳዩና ተጠቃሚነትን በተጨባጭ ያረጋገጡ ስኬቶች መሆናቸውን ተናግሯል።   ወጣት አርሴማ ሽመልስ በበኩሏ ቀደም ባሉት ጊዜያት በከተማዋ በቂ የወጣቶች መዝናኛ ስፍራዎች እንዳልነበሩ አስታውሳ አሁን የተገነቡት ስፍራዎች ለዓይን ማራኪ ከመሆናቸው ባለፈ፣ ወጣቶች ተሰጧቸውን የሚያሳዩበት ሰፊ ዕድል ፈጥሯል ብላለች፡፡      
አካባቢ ጥበቃ
በጣና ሐይቅ ላይ እየተስፋፋ የመጣውን የእምቦጭ አረም ለማጥፋት አዲስ የንቅናቄ ዘመቻ ተጀመረ
Mar 25, 2026 84
ባህር ዳር ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ በጣና ሐይቅ ላይ እየተስፋፋ የመጣውን የእምቦጭ አረም ለማጥፋት አዲስ የንቅናቄ ዘመቻ ተጀመረ። የአማራ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በሐይቁ ህልውና ላይ አደጋ የደቀነውን የእምቦጭ አረም በተደመረ አቅም ለማስወገድ የትብብር ጥሪ አቅርቧል። ከጣና ሃይቅና አካባቢው የእምቦጭ አረምን ለማስወገድ የሚያስችል የንቅናቄ መርሃ ግብር በባህር ዳር ከተማ ሽንብጥ ቀበሌ የጣና ዳርቻ በዛሬው እለት በይፋ ተጀምሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የአማራ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ሃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ፤ በጣና ሃይቅ ላይ እየተስፋፋ የመጣውን የእምቦጭ አረም በተባበረ ክንድ በማስወገድ የሃይቁን ህልውና መጠበቅ ይገባናል ብለዋል።   አረሙን ለማጥፋት በሰው ኃይል እና በማሽን እንዲሁም አጠቃላይ የሕዝቡን ጠንካራ ተሳትፎ ማእከል ያደረገ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል። የእምቦጭ አረም በቀላሉ የመስፋፋትና የማንሰራራት ባሕሪ ያለው በመሆኑ ቀጣይነት ያለው ዘመቻ እና የክትትል ስራ የሚያስፈልግ ስለመሆኑም አፅኖት ሰጥተዋል። በመሆኑም በሐይቁ ህልውና ላይ አደጋ የደቀነውን የእምቦጭ አረም በተደመረ አቅም ለማስወገድ እንዘጋጅ በማለት ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል። የመከላከል ሥራው በሰው ኃይልና በማሽነሪ በመታገዝ እንዲሁም ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በባዮሎጂካል ዘዴ እየተከናወነ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የተያዘውን ሀገራዊ ግብ ማሳካት በሚያስችል መልኩ ዝግጅት እየተደረገ ነው
Mar 25, 2026 90
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ በ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የተያዘውን ሀገራዊ ግብ ማሳካት በሚያስችል መልኩ ውጤታማ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የአረንጓዴ አሻራ የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ(ዶ/ር) ገለጹ። አስተባባሪው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ዘንድሮ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር፣ የመጀመርያው ምዕራፍ ማጠቃለያ ዓመት በመሆኑ ዝግጅቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ በዚህም በዘንድሮው መርሃ-ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ7 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ በላይ ለመትከል እቅድ ተይዞ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት የተገኙ ተሞክሮዎችን በማስፋት የፍራፍሬ ችግኞችን የማስፋት፣ የሀገር በቀል ዝርያዎችን ቁጥር ከፍ የማድረግ ብሎም የእፅዋት አይነት ስብጥር በሰፊው እየተሰራበት መሆኑንም ገልፀዋል። በበጋው ወቅት የተከላ ቦታዎችን የመለየት፣ የተለዩ ቦታዎች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ የማከናወን፣ ከየአካባቢው አየር ንብረት ጋር የሚጣጣሙ ችግኞችን የማፍላትና የተለዩ ቦታዎች ላይ ካርታ የማዘጋጀት ስራ በስፋት መከናወኑን ነው ያስታወቁት።   በዚህም በክልሎች እስካሁን 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለችግኝ ተከላ የሚውሉ ቦታዎችን መለየታቸውን ጠቅሰው እስካሁን ከ110 ሺህ በላይ ችግኝ ጣቢያዎች ወደ ስራ ገብተው ችግኞች እያፈሉ ይገኛሉ ብለዋል። በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ7 ነጥብ 5 ቢሊየን በላይ ችግኝ ለመትከል በእቅድ መያዙን ተናግረው እስካሁን 6 ነጥብ 1 ቢሊየን ችግኝ ዝግጁ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በቀሪው ጊዜ የእንክብካቤ ተግባራት እንደሚከናወኑ ጠቅሰው ጉድጓድ የማዘጋጀት ስራዎችን ጨምሮ ሌሎችም እንደሚከናወኑ ገልጸዋል፡፡ ቀደም ሲል የነበረውን የክረምት ዝናብ ብቻ የመጠበቅ ልምድ መቀየሩን ጠቁመው ይህም ችግኞች ረጅም የዝናብ ወቅት እንዲያገኙ በማድረግ የፅድቀት መጠናቸውን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምረው አስረድተዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አሁን ላይ የህዝቡ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰው በቀጣይም የዜጎችን የባለቤትነት ስሜት የማሳደግ እና የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በክልሉ ከ458 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ተከናውኗል-ቢሮው
Mar 24, 2026 108
‎ባህርዳር ፤መጋቢት 15 /2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በዘንድሮው የበጋ ወራት በአርሶ አደሩ ተሳትፎ በ458 ሺህ 794 ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ መከናወኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ ። ‎የቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ እስመለዓለም ምህረት ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ በዘንድሮ ‎የበጋ ወራት ከዘጠኝ ሺህ የሚበልጡ ተፋሰሶችን መሰረት ያደረገ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ ተካሂዷል። በዚህም ከ458 ሺህ 794 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የማሳና የጋራ ላይ ዕርከን ስራዎችን መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። ‎እንዲሁም ‎ከ91 ሺህ ሄክታር በላይ የተራቆቱና የተጎዱ ተራራማ ቦታዎችን በመከለል ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ተጠብቀው መልሰው እንዲያገግሙ መደረጉንም አመልክተዋል ። በተጨማሪም ‎ከ7 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሚበልጡ የተለያዩ የውሃ ማስረጊያ ስትራክቸሮች መከናወናቸውን ጠቁመው የውሃ ማፋሰሻና መቀልበሻ ቦዮች ግንባታ ስራዎችም መካሄዳቸውን ተናግረዋል ። አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በየጊዜው እየተረዳ በመምጣቱ ከዕቅድ በላይ ስራውን መፈፀም እንደተቻለም አስታውቀዋል። ‎በመጭው የክረምት ወቅት ‎በበጋ ወራት የተከናወነውን የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ በስነ-ህይወታዊ ዘዴ ለማጠናከር ከወዲሁ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል። ‎በምዕራብ ጎጃም ዞን የሰከላ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ዓለሙ ይግዛው እንዳሉት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ መስራት ከተጀመረ ወዲህ የተራቆቱ መሬቶች ደን መልበስ ጀምረዋል ። ‎የእርሻ መሬቶችም የአፈር ለምነታቸው እንዲጨምርና የሰብል ምርታማነት እየተሻሻለ እንዲመጣ ማስቻሉንም ገልፀዋል። ‎‎የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ በየዓመቱ እየሰራን እንገኛለን ያሉት ደግሞ በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የጓንጓ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሙሉነህ ይግዛው ናቸው። ‎ባለፉት ዓመታት በሰራነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ተፋሰሶች በማገገማቸው ለእንስሳት ዋነኛ የመኖ ምንጭ ሆነዋል ብለዋል።  
የሚቲዎሮሎጂ መረጃ አገልግሎትን በማዘመን የሚኖረውን ጠቀሜታ ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Mar 23, 2026 128
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 14/2018 (ኢዜአ)፦የሜቲዎሮሎጂ መረጃ አገልግሎትን ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የተፈጥሮ ሃብት አገልግሎት አቅራቢዎች ለሥነ-ምኅዳር ደኅንነት በይበልጥ ሊተጉ ይገባል ኢንስቲትዩቱ ዓለም አቀፍ የሚቲዎሮሎጂ ቀንን በኢትዮጵያ ለ45ኛ ጊዜ "ዛሬን መመልከት ፤ነገን ለመጠበቅ " በሚል መሪ ሀሳብ እያከበረ ይገኛል።   የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርና በዓለም አቀፉ የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፅህፈት ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ እንደገለጹት፤ የአየር ንብረት ለውጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እያሳደረ ያለ ጉዳይ ነው። በመሆኑም ተፅእኖውን መግታት የሚያስችል የሚቲዎሮሎጂ መረጃ አገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር ዋነኛው ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለውን ፈጣን እድገት ለማስቀጠል የሚቲዎሮሎጂ መረጃ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢኒስቲትዩቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባት ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በተለይም አጋር አካላትን ባሳተፈ መልኩ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥሩ መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ ማዋል እና የሰው ሀይል ልማት ዋና ዋናዎቹ ስለመሆናቸው አንስተዋል።   በኢትዮጵያ ለ45ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሚቲዎሮሎጂ ቀን ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከርና ተደራሽነትን ለማስፋት አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥር አክለዋል። በተጨማሪም ኢንስቲትዩቱ የሚሰጠውን አገልግሎት በዘመናዊ የሚቲዎሮሎጂ ሳይንስ ላይ በመመስረት ዛሬ የተሻለ መረጃ በመያዝ የተሻለ ነገን ለመገንባት የተለያዩ የጥናትና ምርምር ስራዎችን እየሰራ ስለመሆኑን ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የዓለም የውሃ ቀን እየተከበረ ነው 
Mar 22, 2026 121
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ 34ኛው የዓለም የውሃ ቀን ዛሬ በዓለም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። “ውሃ እና ስርዓተ ጾታ” የዘንድሮ መሪ ቃል ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውሃ ቀን ቁልፍ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል። ተመድ የዓለም የውሃ ቀውስ ለሁሉም ሰው የሚተርፍ ቢሆንም ተፅዕኖው ግን እኩል እንዳልሆነ አመልክቷል። ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እና የንጽሕና መጠበቂያ አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብአዊ መብታቸው በማይከበርባቸው ቦታዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነት ጎልቶ እንደሚታይ ገልጿል። በዚህም ሴቶችና ልጃገረዶች የችግሩ ዋነኛ ሰለባ እንደሚሆኑ ጠቅሶ ሴቶችና ልጃገረዶች የውሃ መፍትሔዎች ማዕከል የምናደርግበት ጊዜ አሁን ነው ብሏል። ሴቶች የውሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መቅረጽ አለባቸው ያለው ተመድ ለዚህም የሴቶች ድምፅ፣ አመራር እና ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ነው ያስታወቀው። በዘንድሮው የዓለም ውሃ ቀን ከሚተላለፉ መልዕክቶች አንዱ ውሃ ባለበት እኩልነት ያብባል የሚለው እሳቤ ነው። ሴቶችና ልጃገረዶች በውሃ ውሳኔዎች ላይ እኩል ድምፅ ሲኖራቸው፣ አገልግሎቶቹ ይበልጥ አካታች፣ ቀጣይነት ያላቸው እና ውጤታማ እንደሚሆኑ ተመድ አመልክቷል። ለሁሉም የሚተርፍ ጤናማ፣ የበለጸገ እና እኩልነት የሰፈነበት መጻኢ ጊዜን ለመገንባት፤ የሴቶች የውሃ ዘርፍ አመራር ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችል ስራን ማከናወን እንደሚገባም አስታውቋል። የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። እ.አ.አ 1992 በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የከባቢ አየር እና ልማት ኮንፍረንስ (ሪዮ ኮንፍረንስ) የዓለም መሪዎች የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል። ከኮንፈረንሱ ውጤቶች መካከል አንዱ ውሃን አስመልክቶ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ያተኮረ ቀን የመሰየም ምክረ ሀሳብ ነው። በዚሁ መሰረት ተመድ እ.አ.አ 1992 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማርች 22 እንዲከበር ውሳኔ አስተላልፏል። ውሳኔውን ተከትሎ የዓለም የውሃ ቀን ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዓለም በላይ ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሰዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ። የአየር ንብረት ለውጥ እና ፈጣን የህዝብ እድገት ለውሃ እጥረት ዋንኛ መንስኤዎች ናቸው።
ሀገራት የሴቶች መብቶችን የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባቸዋል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Mar 9, 2026 239
አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት የሴቶች መብቶች እና የሥርዓተ ጾታ እኩልነነት የሚያረጋግጡ ጠንካራ እርምጃዎችን እንዲወስዱ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጥሪ አቀረቡ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። "መብቶች፣ ፍትሕ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሐሳብ ነው። የአፍሪካ ኀብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።   በመልዕክታቸውም፤ ቀኑ የአፍሪካ ሴቶች እና ልጃገረድ ስኬቶችን የምናከብርበት፣ ሴቶችን ማብቃት እና ጥበቃ ላይ የገባናቸውን ቃል ኪዳኖች ዳግም የምናድስበት ነው ብለዋል። ሴቶች በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ከአመራር ሰጪነት እስከ ቴክኒካዊ ቦታዎች ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም አመልክተዋል። የሥርዓተ ጾታ እኩልነት የተቋሙ ሥራ ማዕከል መሆኑንም አስረድተዋል። የአፍሪካ ኅብረትም ቀኑን እያከበረ ሲሆን፤ የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር በአፍሪካ የሴቶችን መብቶች የሚደግፉ ቁልፍ ማዕቀፎችን በዚሁ ወቅት አንስተዋል። ለአብነትም የአፍሪካ ኅብረት የሰው እና ዜጎች መብቶች ቻርተር የሴቶች መብቶች የሕግ ማዕቀፍ፣ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል) እና የሴቶችና ልጃገረዶች ጥቃትን ማስቆም ያለመውን የኅብረቱ ን ኮንቬንሽን በማሳያነት ጠቅሰዋል። የኮንቬንሽኑ ወደ ትግበራ መግባት ትልቅ ስኬት እንደሆነ ገልጸው፤ ሀገራት በሕግ አውጪ ምክር ቤት ማዕቀፉን በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲያስገቡ ጥሪ አቅርበዋል። ሊቀ መንበሩ የሥርዓተ ጾታ እኩልነት እና የልማት የትኩረት መስኮች ቁርኝት እንዳለውም አመላክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የ2026 ትኩረት በሆነው ውኃ እና ንጽህና ጋር በተያያዘ፤ ሀገራት የሴቶችን ጫና የሚያቃልሉ እና ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን እንዲያከናውኑም ጥሪ አቅርበዋል።
በቀጣናው የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው -ኢጋድ
Mar 8, 2026 220
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂን ጨምሮ በቀጣናው የሴቶችን የአመራርና ውሳኔ ሰጪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ማዕቀፎች ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ ለ115ኛ ጊዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው። "መብቶች፣ ፍትህ እና የተግባር ምላሽ፤ ለሁሉም ሴቶች እና ልጃ ገረዶች" የሴቶች ቀን የሚከበርበት መሪ ሀሳብ ነው። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሴቶችን ቀን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፏል። ኢጋድ ለሴቶች አመራር ሰጪነት፣ አይበገሬነት እና በቀጣናው ሰላም፣ ብልጽግና እና ለውጥ ለማምጣት እያበረከቱት ላለው አስተዋጽኦ ክብር እና እውቅና እንደሚሰጥ ገልጿል። በኢጋድ ሴቶች በቀጣናው አመራር ሰጪነት ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። የኢጋድ የሰላም፣ ግብርና፣ ዲጂታል ደህንነት፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና መሬት አስተዳደር ፎረሞች እንዲሁም የኢጋድ የስርዓተ ጾታ ስትራቴጂ ጨምሮ የተለያዩ ኢንሼቲቮች እየተገበረ መሆኑን አመልክቷል። የሴቶች ድምጽ እንዲሰማ እና መሉ ተሳትፏቸው እንዲረጋገጥ የሚያግዙ መድረኮችን መፍጠሩን ነው የኢጋድ ሴክሬተሪያት በመረጃው ያስታወቀው።
ሐተታዎች
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 16, 2026 3256
በዮሐንስ ደርበው ባሳለፍነው ሳምንት … የጤና ነገር … የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በየአዝማናቱ ሕዝብን በኅብረት ያሥተሣሠሩ ክስተቶች ይስተዋላሉ። ታሪክ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን በየጊዜው አንድ በሚያደርጓቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መለያየት አይሆንላቸውም። እንደውም በመሃላቸው የሚከሰቱ አለመግባባቶች ሁሉ እንደጉም ተነው በጋራ መቆም የሠርክ ተግባራቸው ነው። በዓድዋ፣ በካራማራ እና በሌሎችም ስፍራዎች ያደረጓቸውን ፀረ ባዕዳን ትግል ጨምሮ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ባሉት የልማት ሥራዎች ያስመዘገቧቸው ድሎች በማሳያነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት የሚካተቱ ናቸው። እነዚህ የኢትዮጵያን ኅልውና ለማስጠበቅ ሕዝቡ በአንድነት በመሰለፉ የተቀዳቻቸው ድሎች ናቸው። አንድነት ባይኖር ድሎቹ አይታሰቡም። የጀግኖች አያቶቻቸው ልጆች በዚህ ዘመንም ትልቅ ድል አስመዝግበዋል፤ በቀጣይ ደግሞ ሌላ። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት የተገለጠበት ዘርፈ-ብዙ ፀጋ ካላቸው ላይ ዕጃቸውን ያልሰበሰቡ፤ ኪሳቸውንም ያልዘጉ ኢትዮጵያውያን፤ በቁጭት፣ በደም፣ በላብ እና በጥሪታቸው ሀገራቸውን በክብር ያስጠራ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የመሰለ ሜጋ ፕሮጀክት ገነቡ። ፍሬውንም ማጣጣም ከጀመሩ ሰነባበቱ። ይህ ጥቅመ-ብዙ ግድብ ከቀዳሚ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የተሻገሩ በርካታ ትሩፋቶች አሉት። አንድነትን በማጠናከር ረገድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በተደፈረ ጊዜ በዓድዋ ዘመቻ ወገን በኀብረት እንደቆመው ሁሉ፤ የሕዳሴው ግድብ በግንባታ ጊዜው የሀገሬው ኅብረት ማሠሪያ ሆኗል። በዚህ ዘመንም ለአንድ ዓላማ መቆምን በማስረጽ የራሱን ዐሻራ አኑሯል። የሀገራቸውን ብልጽግና በሚሹ ታታሪዎች ርብርብ እንደመገንባቱ፤ ከምረቃ በኋላም የሚጠበቅበትን የኤሌክትሪክ ኃይል በማምረት ለሁሉም መሆኑን በተግባር አሳየ። ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ ባሏት የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ተደማሪ መስኅብ ሆነ። ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ ያለው ፍሰት እየጎመራ የሕዝቡ ተጠቃሚነት እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ይገኛል። እንደ ዜጋ ግድቡ በቁርጠኝነትና በብልኅ አመራርነት ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛል፤ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የጎብኝ መዳረሻ መሆኑ ደግሞ ተጨማሪ ፀጋ። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ አንድም አካባቢውን በመጎብኘት እንዲሁም ለጎብኝ ምቹ ሁኔታዎችን በማስፋፋት። ምክንያቱም፤ የግድቡ ታሪካዊ አሠራር …ቁጭቱ…ቁርጠኝነቱ…አንድነቱ ... ራሱን የቻለ ታሪክ ነውና ይህን ሠንዶ ለጎብኝዎች በሚሆን መልክ ማንበር ያስፈልጋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይስ? በሀገሪቱም በአኅጉሪቱም በዘርፉ ሜጋ የሆነውን ይህን ፕሮጀክት ለመልከ-ብዙ ፈተናዎች ሳይበገሩ በስኬት የቋጩ የዓድዋ እና ካራማራ ድሎች ባለቤት የሆኑት የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ እንደ ባሕር በር ባለቤትነት ባሉ ትላልቅ የኅልውና ጉዳዮች ላይ ሊገለጥም ይገባል። የባሕር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው። የሕዝብ ጉዳይ ነው። በዚህ ጉዳይ ቅንጣት ልዩነት አያሻም። “ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር” ነውና ብኂሉ… ተባብሮ ኅልውናን ማስቀጠል እንጂ…. ደግሞም ይህ ታሪካዊ ስህተትን የማረቅ ሂደት ነው። በታሪክ፣ በሠነድ እና በሌሎችም ማሥረጃዎች ኢትዮጵያ ሐቅ አላትና። በጥቃቅን ነገሮች የማይጠቅም የልዩነት በርን መክፈት አያሻም። ብርቱዎቹ ለልዩነት ዕድል ያልሰጡት በዓድዋ በካራማራ በኅብረት አንጸባራቂ ድል ተጎናጽፈዋል። የአሁኑ ትውልድም ኅልውናውን ለማቆየት የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ ይለዋል። ታሪክን መዘከር ተገቢ ነው፤ ጠብቆ በማቆየት መማርም። አሁንም ዳግም ታሪክ መሥራት ይገባል። ለዚህም በቁጭት መነሳት…የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ። #ዓድዋ #ካራማራ #የብርቱዎቹ_ልጆች_ብርታት #ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ #የባሕር_በር #ቀይ_ባሕር #የትውልድ_ጥያቄ #በኢዜአ_ዐይን
ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ለቀጣናው ይዞት የመጣው ተስፋ 
Mar 2, 2026 347
በሙሴ መለሰ(ኢዜአ) የአየር ንብረት ቀውስ በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ይህም በቀጣናው ግብርና እና ስርዓተ ምግብ ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። ኢ-ተገማች የዝናብ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚከሰቱ ድርቆች እና የመሬት መራቆት የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ፣ በዜጎች ኑሮ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እና የስርዓተ ምግብ ላይ ፈተና መሆኑን ቀጥሏል። ግብርና በምስራቅ አፍሪካ ከ25 እስከ 40 በመቶ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) የሚሸፍን ነው። የግብርናውን አብዛኛውን ድርሻ የሚወስዱት አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ናቸው። በነዚህ ሀገራት ግብርና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ድርሻ ይወስዳል። በቀጣናው ያለው ግብርና አብዛኛው ዝናብ ላይ ጥገኛ በመሆኑ በየጊዜው ለሚቀያየረው የአየር ንብረት ሁኔታ እና አደጋዎች ተጋላጭ ነው። ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋሙ ስትራቴጂዎች እና ስልቶች መቅረጽና መተግበር ላይ ውስንነቶች አሉ። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ጠንካራ የግብርና ስርዓት ለመገንባት በአፍሪካ ደረጃ እየተተገበሩ ካሉ ተግባራት መካከል አንዱ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) ሁሉን አቀፍ እይታ ያለው የግብርና ምርታማነት አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ይህ የአሰራር ዘዴ የግብርና ምርታማነት ብቻ ሳይሆን ለአደጋዎች የማይበገር አቅም መገንባት እና ለአየር ንብረት ተስማሚ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ጽንሰ ሀሳቡ ከተለምዷዊ የግብርና አሰራር በመውጣት ሳይንስ፣ ፖሊሲ፣ ፋይናንስ እና ቴክኖሎጂን በማጣመር ግብርናን የማይበገር፣ ዘላቂ እና የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን ማላቅ እንደሚገባ ያመለክታል። ምርታማነት እና ገቢ መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አቅም መገንባት እንዲሁም የማጣጣሚያ እቅዶችን መተግበርን ጨምሮ የበካይ ጋዞችን ልቀት መቀነስ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ቁልፍ የሚባሉ ምሰሶዎች ናቸው። በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና (Climate-smart agriculture) አማካኝነት በቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ እና ሌሎች ድርቅና ከፍተኛ ሙቀትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን በመትከል ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በአፍሪካ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል። የውሃ እና አፈር አስተዳደርን ማሻሻል፣ ውጤታማ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ዲጂታል የአየር ንብረት የማማከር አገልግሎቶችን (digital climate advisory services) መስፋት ምርታማነትን በመጨመር እና አርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ እያገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክ የአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና ኢኖቬሽን ስራዎች ተደራሽ እንዲሆኑ ያደረገ ሲሆን ምርት በ25 ሚሊዮን ቶን እንዲጨምር አስችሏል። በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ ኢኒሼቲቮችን በመተግበር ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ብዝሃ ህይወት እና አካባቢን እንዲጠብቁ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። አረንጓዴ አሻራ የዚሁ ስራ አንድ ማሳያ ነው። ለአየር ንብረት ተስማሚ የሆነ ግብርና (Climate-smart agriculture) በምስራቅ አፍሪካ ላለው የአየር ንብረት ቀውስ እንደ ስትራቴጂካዊ ምላሽ መስጫ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ዘላቂ ፈተና በሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ይህ የግብርና አሰራር ዘዴ አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይነሳል። ድርቅን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መጠቀም፣ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የተቀናጀ የደን ልማት ስራ፣ የውሃ አስተዳደርን ማሻሻል፣ አርብቶ አደሮች በሚኖርባቸው አካባቢዎች የማይበገር የአደጋ መቋቋም ስርዓትን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት መረጃውን በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ እና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓትን ማጠናከር እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች መካከል ይጠቀሳሉ። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የምግብ ስርዓት የማይበገር ፕሮግራም (FSRP) ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ትኩረት ከሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና እና የስርዓተ ምግብ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ስብሰባ ይደረጋል።   የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በአፍሪካ ቀንድ ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ የምክክር ፎረም የካቲት 24 እና 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሥርዓተ ምግብ አይበገሬነት ፕሮግራም ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቢሮ እና ከደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል ጋር በመሆን ፎረሙን አዘጋጅተውታል። ምክክሩ የአየር ንብረት ለውጥ ግብርና ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ባለበት ወቅት የሚካሄድ መሆኑ ወቅቱን የጠበቀ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ከአደጋ ጊዜ ምላሾች ወደ ረጅም ጊዜ የማይበገር ስትራቴጂዎች እና ከሙከራ ጊዜ ኢኒሼቲቮች ወደ ቀጣናዊ መፍትሄዎች መሸጋገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከኢጋድ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የልማት አጋሮች፣ ተመራማሪዎች እና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። በቀጣናው የሥርዓተ ምግብን ማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን ማስፋት የሚቻልባቸውን ተጨባጭ መፍትሄዎች እንደሚዳሠሡም ተመላክቷል።   የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የማይበገር፣ አካታች እና ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የግብርና ሥርዓቶችን ከምግብ ምርታማነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ጎን ለጎን መገንባት የሚቻልበትን መደላድል መፍጠር ከፎረሙ የሚጠበቅ ዋና ውጤት ነው ተብሏል። ቀጣናዊ ፎረሙ ኢጋድ ተጋላጭነትን ወደ እድል ለመቀየር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ለመስጠትና ለግብርና ኢኖቬሽን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም አመልክቷል። በአፍሪካ ቀንድ ሚሊዮኖች የአየር ንብረት ለውጥ በፈጠራቸው ቀውሶች ገፈት ቀማሽ በሆኑበት በአሁኑ ወቅት ለአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የቴክኒክ አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የግብርና አሰራር ዘዴው ለዘላቂ ልማት፣ ለኢኮኖሚ አይበገሬነት እና ማህበራዊ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ እንደሆነም በዘርፉ ባለሙያዎች ይነሳል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው ቀጣናዊ ፎረም በአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የሀገራትን የፖለቲካ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ለማጠናከር እና ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ መልካም አጋጣሚ የሚታይ መድረክ ነው። በተለይም ለአየር ንብረት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የሚከናወነው ስራ የማይበገር አቅምን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በቀጣናው የሚደረጉ ጥረቶች ከንግግር ባለፈ በተግባር ታግዘው ውጤታማ ከሆኑ ከተበታተኑና አደጋን ማዕከል ካደረጉ ምላሾች ወደ የማይበገር፣ አካታች እና መጪውን ጊዜ የዋጀ የግብርና እድገት መሸጋገር ይቻላል።
የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና !
Feb 24, 2026 401
(በፋኑኤል ዳዊት፤ ከሀዋሳ ኢዜአ ቅርንጫፍ) ሀዋሳ፤ የካቲት 17/2018 (ኢዜአ):- የባህር በር ለቀጣናዊ ሰላም፤ ለአህጉራዊ ብልፅግና ! የባህር በር የአንድ ሀገር መሬት በቀጥታ ከውቅያኖስ ወይም ከባህር ጋር የሚገናኝበት ዳርቻ ሲሆን አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ ግንኙቶች የሚከናወኑበት መተላለፊያም ነው። የባህር በር ከንግድና ከሌሎች የኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነትና ትስስር የቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ጸጥታንና አስተማማኝ ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልህ እንደሆነ ይገለጻል። ስለዚህም ነው የባህር በር የህልውና ጉዳይ ተደርጎ የሚወሰደውና የባህር በር አልባ ሀገር መሆን እንደ ከባድ ችግር የሚታየው። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከሚጋፈጧቸው በርካታ ችግሮች መካከል የሸቀጦች የምልልስ ጊዜ ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን ያሳድራል። በዚህም ሳቢያ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በትራንስፖርትና በማሪታይም ንግድ በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ ይሆናሉ። ይህም ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ ስለሚያስገድድ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ተጽዕኖው ይጎላል። ጥገኝነቱ ለጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና አለመረጋጋት የማጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። በአንዱ ሀገር የሚነሳው የፖለቲካ ትኩሳት ወይም የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም የባህር በር የሌለውን ሀገር ሳይወድ በግድ ሰለባ የማድረግ ወይም ተፅዕኖ የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ከባህር በር ተነጥላ የማታውቀው ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ ለዘመናት የባህር በር አልባ ሀገር የመሆን ክስተት በማስተናገዷ ከላይ በጥቂቱ የጠቀስናቸውን ችግሮች ስትጋፈጠው ቆይታ ዛሬ ላይ ደርሳለች፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ ሁሌም ህዝቡን ሲቆጨውና ሲያንገበግበው የቆየ ጉዳይ ሲሆን በጥቂት ግለሰቦች ይሁንታ የተቸረ ሀገርን ዝግ አድርጎ የማቆየት ሴራ ነው። ይህ ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ የቆየውን የባህር በር የማግኘት ፍላጎት ገሃድ ያወጣ የትውልዱ ጥያቄ እንዲሆን አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ይፋ በማድረግ ትውልዱ በውስጡ ይዞት የኖረውን ቁጭት ግልጽ እንዲወጣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 65ኛ ዓመቱን ባከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከታች ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ የሚያጋጥሙ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚችልና ለቀጣናዊ ሰላም የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው አክለው እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ብሎም ለአፍሪካ ብልፅግና የሚሰራ ተቋም እየገነባች መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጠቀሜታው ለገረቤት ሃገራትና ለሌሎችም መሆኑን በግልፅ አስቀምጠዋል። በጉዳዩ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እንደገለፁትም፤ ኢትዮጵያ በዘመናት ታሪኳ ተነጥላ ከማታውቀው የባህር በር ባለቤትነት በታሪክ ላለፉት 30 ዓመታት ተገልላ መቆየቷ ለጂኦ ፖለቲካዊና ጂኦ ኢኮኖሚክስ ችግሮች አጋልጧታል፡፡ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዲፕሎማሲ አሰልጣኝና የውጭ ፖሊሲ ተመራማሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ (ዶ/ር) በመንግስትነትና ከባህር በር ሳትነጠል ለዘመናት የኖረች ሀገር በሴራ ፖለቲካ ዝግ ሀገር እንድትሆን መደረጉ የታሪክ ስህተት መሆኑን አንስተዋል። የዓለም ሀገራት በተለያየ ምክንያት ከባህር በር እንዳይገለሉ የሚያስቀምጡት ህጎች ቢኖሩም የኢትዮጵያ በቅርብ ርቀት ከዓለም ጋር በቀጥታ እንዳትገናኝ፣ የባህር በር አልባ ሀገር እንድትሆን መደረጉ ተቀባይነት የሌለውና በትውልዱ ዘንድ ምላሽ አጥቶ የተቀመጠ ጥያቄ ነው ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ደመቀ አጭሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ጥያቄው የትውልድ መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ በሴራና አግባብ ባልሆነ መንገድ የባህር በር ባለቤትነትን እንዳጣች ነው የሚናገሩት፡፡ ያለፈው ስርዓት የባህር በር ጉዳይን በግልም ይሁን በቡድን እንዲነሳ ባለመፈለጉ ውስጥ ውስጡን የቆየውን ይህ ጉዳይ አሁን ላይ መንግስት ኃላፊነትን ወስዶ እስከ መቼ ተዘግተን እንኖራለን ብሎ በይፋ ማንሳቱ ወሳኝና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ምሁሩ አንሰተዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቅማ የውጭ ግንኙነቶችን፣ ንግድና እንዲሁም በዚህም በቀጠናው ተፅዕኖ የመፍጠር ሀይል እንደነበራት አውስተው ከባህር በር በተለይም ከቀይ ባህር ተነጥላ አትታይም ያሉት ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ንጉስ በላይ (ዶ/ር) ናቸው። ይሁን እንጂ ከአውሮፓ ቅኝ ገዢ ሀገራት መካከል ኢጣሊያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1890 ዎቹ ጀምሮ እስከ 1950 ዎቹ ኤርትራን በመግዛቷ ከባህር በር ለመገለል አደጋ የዳረጋት ክስተት አጋጥሟት እንደነበር እና ይህም በታሪኳ ዝግ ሀገር እንድትሆን ማድረጉን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1952 ጀምሮ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን በመዋሃዷ የባህር በር ባለቤትነት መብት ድጋሚ እንድታገኝ በማድረግ እስከ 1991 ድረስ ተጠቃሚ እንደነበረች አንስተዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዳልካቸው ጀንበሬ (ዶ/ር) በታሪኳ ከቀይ ባህር ተነጥላ የማታውቀው ሀገር ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት ጥያቄ ለመመለስ ሲባል የባህር በርን ሙሉ በሙሉ እንድታጣ መደረጉ ፈጽሞ ተገቢነት የሌለውና ፈጣን ምላሽ የሚሻ የትውልዱ የቁጭት ጥያቄ ነው ብለዋል። በተለይም ኢህአደግ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ይህ ጉዳይ እንደ ጥያቄ ማንሳት እንደወንጀል የሚታይ ሆኖ መዝለቁ ስርዓቱ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት ባለፈ ታሪክንና የሀገሪቷን የመጻኢ ዕጣ ፈንታ ያልተመለከተ መሆኑ ጥያቄ ሲያስነሳበት እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለወደብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ከብሔራዊ ጥቅም ጋር በቀጥታ የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት አምባሳደር ማርቆስ (ዶ/ር) በተፈጠረ የፖለቲካ ስህተት ከባህር ተዘግታ መቆየቷ አግባብ ስላልሆነ ጉዳዩ ፈጣን ምላሽን ይሻል ብለዋል። ለዚህም በፖለቲካ ስህተትና በሴራ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት ጥያቄ እንዲመለስላት የዓለም ማህበረሰብ ጉዳዩን በግልጽ እንዲያውቀው ለማድረግ በተሰራ ስራ በጎ ምላሽ እየተገኘበት ነው ብለዋል። ተገቢ ባልሆነ መንገድ የታጣውን የባህር በር ማግኘት የትውልዱ የዘመናት የቁጭት ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ መንግስት በቁርጠኝነት የጀመረውን የዲፕሎማሲ ጥረት አድንቀዋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ለሚበራከቱበት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ሀገራቱ ላላቸው ተያይዝ የመበልፀግ ራዕይ መሳካት ወሳኝ ድርሻ ስላለው የጎረቤት ሀገራት ለጥያቄው በጎ ምላሽ ይሰጣሉ ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል። የባህር በር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ፣ ለወታደራዊ ሀይል ፣ ለማናቸውም የውጭ ግንኙነት እንቅስቃሴ መሳለጥ ተኪ የለሌለው እንደሆነ ያነሱት ደመቀ(ዶ/ር) ለኢትዮጵያ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ እንዲሁም የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ እንደሆነ አንስተው የተለያዩ ስልቶች በመከተል ዕድሎችን ለመጠቀም የተጀመረውን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ምሁሩ አክለውም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የተሳሰሩ የጎረቤት ሀገራትም በጉዳዩ ዙሪያ በጎ ምላሽ በመስጠት ሊተባበሩ እንደሚገባ ጠቅሰው የኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ለቀጣናው ብሎም ለአህጉሩ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ለጥያቄው ድጋፋቸውን ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚገኙ ሀገራት ያላቸውን ጥያቄ በፍትሃዊነትና በአግባቡ እየመለሱ ተያይዞ የመበልፀግ ዕድልን ለመጠቀም የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለሁሉም ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱትና ሊቀበሉት ይገባል ያሉት ደግሞ ንጉስ (ዶ/ር) ናቸው። የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር የተሳሰረና መነጣጠል የማይቻል እንደሆነ የሚገልፁት ምሁሩ ይህም ያላቸውን ዕምቅ አቅም አቀናጅተው እንዲጠቀሙና ፍላጎታቸውን እንዲያሟሉ የማድረግ ዕድልን የሚያሰፋ፤ ቀጣናውንም የተረጋጋ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል ። የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ ለማንም የምንተወው አይደለም ትውልዱ እንዲመለስ የሚፈልገው ጥያቄ ነው ያሉት እንዳልካቸው (ዶ/ር) መንግስት በይፋ መጠየቁን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲፕሎማሲ የተጀመሩ ጥረቶች እያስገኟቸው ያሉ በጎ ምላሾችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ምሁሩ አክለውም ያለውን አለም አቀፍ በጎ ምላሽ ከግምት በማስገባትም የአፍሪካ ቀንድም ሆኑ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ቀጣናዊ ብሎም በዚህ ውስጥ አህጉራዊ ብልፅግናን ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት።      
   የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ
Feb 14, 2026 379
በሙሴ መለሰ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ (Assembly of Heads of State and Government) የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የፖሊሲ እና የውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ይህ አካል ከሁሉም አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግስታት ወይም የሀገራት መሪዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች የመቅረፅ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል። በአፍሪካ ህብረት ድረ-ገጽ ላይ በቀረበው መረጃ መሰረት፣ የጉባኤው ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦ የፖሊሲ አቅጣጫዎች፦ የህብረቱን የጋራ ፖሊሲዎች መወሰን፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየት እና ዓመታዊ የሥራ መርሐ-ግብሮችን ያጸድቃል። ውሳኔ አሰጣጥ፦ በአህጉራዊ ሰላም፣ ጸጥታ እና ልማት ላይ የመጨረሻ ውሳኔዎችን ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ፦ የህብረቱን ፖሊሲዎች እና ውሳኔዎች አፈጻጸም መከታተል፣ እንዲሁም አባል ሀገራት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል። ሹመቶች፦ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና ኮሚሽነሮችን ይሾማል። ጣልቃ ገብነት፦ በአባል ሀገራት ውስጥ የጦር ወንጀል፣ የዘር ማጥፋት ወይም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ጣልቃ የመግባት ውሳኔ ያሳልፋል። ክትትልና ግምገማ: የህብረቱን አካላት እና የስራ አፈጻጸም ይገመግማል። በጀት እና መዋቅር፦ የህብረቱን በጀት ማጽደቅ፣ እንዲሁም የኮሚሽኑን አደረጃጀት እና ደንቦችን መወሰን።   የጉባኤው አወቃቀር እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት አባልነት፦ ጉባኤው የሁሉንም 55 አባል ሀገራት መሪዎች ወይም ሕጋዊ ተወካዮቻቸውን ያቀፈ ነው። የውሳኔ አሰጣጥ፦ ውሳኔዎች የሚሳለፉት በስምምነት (Consensus) ሲሆን፣ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ግን በሁለት ሦስተኛ (2/3) ድምፅ ይወሰናሉ። የአሰራር ጉዳዮች ደግሞ በቀላል አብላጫ ድምፅ ይጸድቃሉ። ምልዓተ ጉባኤ (Quorum)፦ ማንኛውንም ስብሰባ ለማካሄድ ቢያንስ ሁለት ሦስተኛው የአባል ሀገራት ተወካዮች መገኘት አለባቸው።   የጉባኤው ቢሮ (Bureau) ጉባኤው በየዓመቱ የሚመረጥ አንድ ሊቀመንበር እና ሌሎች አራት አባላት (ምክትል ሊቀመንበሮች) ያሉት ቢሮ አለው። ይህ ቢሮ የአህጉሪቱን አምስቱንም ቀጣናዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና መካከለኛ አፍሪካ) ተዋጽኦ የጠበቀ መሆን ይኖርበታል።   የጉባኤው አሠራር እና መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች መደበኛ ስብሰባ፦ ጉባኤው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል። ልዩ ስብሰባ (Extraordinary Session)፦ ማንኛውም አባል ሀገር ጥያቄ አቅርቦ በሁለት ሦስተኛ አባል ሀገራት ድጋፍ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ልዩ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል። ውሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ፦ ጉባኤው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች በአባል ሀገራት ተፈጻሚ መሆናቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት።   የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች የኮሚሽኑ ሊቀመንበር፦ መሐሙድ አሊ ዩሱፍ (ጅቡቲ) እ.አ.አ በየካቲት 2025 ተመርጠው በአሁኑ ወቅት የህብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎች የሚመራውን ኮሚሽን እየመሩ ይገኛሉ። ምክትል ሊቀመንበር፦ አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሃዳዲ (አልጄሪያ) የኮሚሽኑ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው። በተለያዩ ዘርፎች የሚሰሩ ስድስት ኮሚሽነሮች በህብረቱ የስራ አስፈጻሚ ክንፍ በሆነው ኮሚሽን እየሰሩ ነው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል። ከፍተኛው የውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው ጉባኤው በተለያዩ አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 21, 2026 712
ከመጋቢት 6 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ማሳሰቢያ በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ስለዚህ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በኃላፊነት ልንጠቀም ይገባል ሲሉ ያሳሰቡት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ባሳለፍነው ሳምንት … ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል ፕሬዚዳንት ታዬ ያስጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ባሳለፍነው ሳምንት የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑን ገልጸው፤ የሕይወት ምሉዕነት የሚረጋገጠው ካለው ላይ ቆርሶ በመስጠት መሆኑን አስገንዝበዋል። ለተቸገሩ መድረስና ለወገን መቆም ትልቅ የመንፈስ ዕርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ መጠናከር እንዳለበትም አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ የተወያዩት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጉብኝት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በእንዶዴ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያ እና በኤ ኤም ጂ (AMG) - እንዶዴ የባቡር መሥመር ፕሮጀክቶች ላይ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። እነዚህ በራስ ዐቅም የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነታችንን ከማሻሻል ባለፈ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን ያጸናሉ ሲሉም በዚሁ ወቅት በአጽንዖት ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ-መሥተዳድሮች ጋር በሌላ በኩል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል ርዕሳነ መሥተዳድሮች፣ ከከተማ አሥተዳደር ከንቲባዎች፣ ከትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጂታል ፈተና ምዘና ሥርዓት እና የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታን በተመለከተ በበይነ መረብ ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ትግበራ ለማሸጋገርና ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ የምዘና ሥርዓት ለመገንባት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ስታንዳርድ 1 ሺህ 452 ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መጪው ነሐሴ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሙስሊሞች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ረመዳን ወር ተጠናቅቆ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት የተከበረው ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። ለበዓሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች የፌደራል፣ የከተማ አሥተዳደሮች እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። #ባሳለፍነው_ሣምንት #ኢዜአ
በኢዜአ ዐይን …!
Mar 21, 2026 188
በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ (በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማስፋፋት ስትወጥን የቀደመ ወረቷን፤ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶቿን ይዛ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ የተሰኙ ትላልቅ ኢኒሼቲቮችን ቀረጸች። ይህን ዕውን ለማድረግ ስትዘይድም የሕዝቧን የፋይናንስ፣ የዕውቀት እና የጉልበት ዐቅም በመደመር መጠቀምን ሻተች። በዚህም መሠረት በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ኢኒሼቲቮች በርካታ ስኬቶችን አስመዘገበች። ትሩፋታቸውም ሰፊ አበርክቷቸውም በርካታ ሆኖ ብቅ ብሏል። በኢዜአ ዐይን …! ✍️ ገበታ ለሸገር በአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻዎችና መናፈሻዎችን ለማልማት በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረገው ገበታ ለሸገር ኢኒሼቲቭ፤ ከእንጦጦ ተራራ እስከ አቃቂ ወንዝ ያለውን የሚሸፍን ነው። የሚሠራበትን ገንዘብ ለማሰባሰብም የገበታ ለሸገር የእራት ምሽት በዳግማዊ አጼ ምኒልክ የግብር አዳራሽ ተዘጋጀ፤ ባለሀብቶች፣ የንግድ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ጨምሮ ዓለም አቀፍና አኅጉራዊ ድርጅቶችም ተሳትፈዋል። ኢኒሼቲቩ አንድነት ፓርክን ጨምሮ የእንጦጦ መናፈሻንና ሌሎች የተለያዩ መዲናዋን ያስዋቡ በረከቶችን ችሯል። ይህም የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ሃብት በማልማት በርካታ ቱሪስቶችን ከመሳብ ባለፈ፤ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለምጣኔ ሃብት ዕድገት ጉልኅ አስተዋጽዖ አበርክቷል። ለዚህ ሁሉ ስኬት መነሻ የሆኑትን ጉዳዮች ያስጀመሩትም ያስፈጸሙትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በገበታ ለሸገር የተገኙ ውጤቶችን መነሻ በማድረግ ገበታ ለሀገር የተሰኘውን ኢኒሼቲቭ አበሠሩ። ✍️ ገበታ ለሀገር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነሐሴ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻን ለማልማት ያለመ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አዘጋጅተዋል። ይህም በአዲስ አበባ ከተሠራው ገበታ ለሸገር ቀጥሎ የተከናወነ ነው። በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የገበታ ለሀገር ዓላማ የተለያዩ አካላትን በማሳተፍ የቱሪስት መስኅብ የሚሆኑና የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ አካባቢዎችን ማዘጋጀት መሆኑን አስገንዝበዋል። በገበታ ለሀገር መርሐ-ግብር ባለሀብቶችን ጨምሮ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ 3 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን መግለጻቸው ይታወሳል። ይህን ለማሳካት የሀገሪቱን ባለሃብቶች፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች በተለያዩ መርሐ-ግብሮች የተሳተፉበት የገቢ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ውጤታማ ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገበታ ለሀገር ውጥን፤ እንደ ሀላላ ኬላ፣ ጨበራ ጩርጩራ፣ ወንጪ እና ጎርጎራ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና የተፈጥሮ ሀብቶችን አጉልተው በማሳየት ይበል ያሰኘ ውጤት አስመዝግቧል። ✍️ ገበታ ለትውልድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2015 ዓ.ም ገበታ ለትውልድ የተሰኘ ኢኒሼቲቭ ይፋ ያደረጉ ሲሆን፤ ይህም ተጨማሪ መዳረሻዎች እንዲለሙ አስችሏል። በዚህ ኢኒሼቲቭ ሥር በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በአፋርና ሶማሌ ክልሎች የመዳረሻ ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል፤ እየተከናወኑም ነው። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዳሴ ግድብ አካባቢና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የፕሮጀክቱ አካል የሆኑ የቱሪዝም መዳረሻ ሥፍራዎች እየለሙ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውን የሸበሌ ሪዞርት በይፋ መርቀዋል። እያንዳንዱ የሪዞርቱ ገጽታ የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ባህላዊ ሐብት የሚያንፀባርቅ ነው። ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በሚደረገው ጉዞ ትልቅ ታሪካዊ እጥፋት እንደሆነም ተገልጿል። ሎጎ ሐይቅ ሪዞርትም ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመረቀ ሲሆን፤ ለጎብኚዎች የማይረሳ ትውስታን የሚሰጥ እጅግ ማራኪ ቦታ ሆኖ ቀርቧል። ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለመሆን ያላትን ቁርጠኝነትና ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ቋሚ ምስክርም ነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት። የቱሪዝም ልማቱን ከተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ፣ ከዘላቂነትና ከአካታችነት ጋር በማቀናጀት፤ ሪዞርቱ የወሎ ሕዝብ ያለውን ጥልቅ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ዕሴት ለዓለም ማኅበረሰብ የሚያስተዋውቅበት ሰፊ ገበታ ሆኖ ያገለግላል። ታሪካዊ ቦታዎችና የሀገር መገለጫ መሠረተ-ልማቶች ብሔራዊ ትርክቶችንም የሚገነቡ ናቸው። በአጠቃላይ እነዚህ ሁሉ ጥረቶች ለአካባቢ ጥበቃ ቅድሚያ በመስጠት ብሎም በየአካባቢው የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል። የቱሪዝም ዘርፉን ለማጎልበት፣ ብዙ ጎብኚዎችን ለመሳብ፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማጠናከር፣ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ መዳረሻዎችን ለማልማትና ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው። እንዲሁም ነባር ቅርሶችን በማደስና በመጠገን ለትውልድ ለማሻገር ደማቅ ዐሻራ አሳርፈዋል። በሌላ በኩል የቱሪዝም መዳረሻዎችን ማልማት የመንግሥት ብቻ እንዳልሆነ ዐሳይተዋል። ባለሀብቶችና ሌሎች የማኅበረሰብ ክፍሎችም ሀገራቸውን የመሥራት ሚና እንደሚጠበቅባቸው አሥተምረዋል። ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት ብሎም በርካታ የሥራ ዕድሎች በመፍጠር በኢኮኖሚው ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በኢትዮጵያም ቱሪዝም መንግሥት ላስጀመረው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የማዕዘን ድንጋይ ነው። ከአምስቱ ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎችም አንዱ የሆነው ለዚህ ነው። መሠረተ-ልማቶች ከሚገነቡባቸው ጡቦች ባለፈ የነገን ሀገራዊ ማንነት፣ ራዕይ እና መዳረሻን ይበይናሉ። ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ እንኳንም ታሰቡ፤ እንኳንም ተሳኩ። ይህ ባይሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ተጨማሪ መዳረሻ ባላገኘች ነበር።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Mar 14, 2026 1398
ከየካቲት 29 - መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … ✍️ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምሥራቅ ኢትዮጵያ • ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በድሬዳዋ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተመልክተዋል። ማዕከሉ በውስጡ 10 ተቋማት ይዞ 73 የሚሆኑ አገልግሎቶችን ለዜጎች እየሰጠ መሆኑንም ገልፀዋል። ከሳምንቱ ዐበይት ክንውኖች መካከል • በተመሳሳይ በድሬዳዋ የተስማሚነት ምዘና ድርጅትን ጎብኝተዋል። ድርጅቱ ዓለም አቀፍ የአሠራር ሥርዓትን በመከተል ለአምራቾች፣ ለአገልግሎት ሰጪዎች፣ ለላኪዎች፣ ለአስመጪዎች፣ ለተቆጣጣሪ መሥሪያ ቤቶች፣ ለምርምር ተቋማትና ለሸማቹ ማኅበረሰብ የምርትና አገልግሎቶች የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም ተናግረዋል። • የድሬዳዋ የኮሪደር ልማትንም የጎበኙ ሲሆን፤ የኮሪደር ልማቱ ምቹ የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች፣ የተሻሻለ የአካባቢ ውበትን እና ጥራታቸውን የጠበቁ የማኅበረሰብ መሰብሰቢያ ስፍራዎች በድሬዳዋ ዕውን እንዲሆኑ ማስቻሉን አስረድተዋል። • ከድሬዳዋ ነዋሪዎች ጋርም የረመዳን ኢፍጣር መርሐ-ግብር ያከናወኑት ባለፈው ሳምንት ነው። • በድሬዳዋ የሚገኘውን እመርታ ቤተ-መጻሕፍትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጎብኝተዋል። ቤተ-መጻሕፍቱ በአንድ ጊዜ ለ1 ሺህ ሰው አገልግሎት መስጠት እንደሚችል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። • በሳምንቱ መጀመሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሐረሪ ክልል ሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተሠራውን የገጠር ኮሪደር ሥራ ተመልክተዋል። የአካባቢው ነዋሪ በንቃት የተሳተፈበት የገጠር ኮሪደር ሥራ፤ ባሕላዊ የግንባታ ዘዴን፣ የተደራጀ ዕቅድ እና ተግባራዊ የአሠራር ውጤት ያሳየ መሆኑን አብራርተዋል። • የቁንድዶ ተራሮችንም ጎብኝተዋል። • በሐረር ከተማ የተቋቋመውን መሶብ የአንድ ማዕከልም ተመልክተዋል። ማዕከሉ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል አቀናጅቶ የማቅረብ ሀገር ዐቀፍ መርሐ-ግብር አካል መሆኑንም አስገንዝበዋል። • በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን መልካ በሎ ወረዳ የሚገኘውን ናሲኦል ዋሻም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት ጎብኝተዋል። • ከሐረር ከተማ ነዋሪዎች ጋርም የረመዳን ኢፍጣር አካሂደዋል። ✍️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሹመት መስጠታቸው • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ ሌ/ጄኔራል አሥራት ደኔሮን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር፣ ረዳት ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድን እና አቶ ኤርዚቅ ኢሳን የአዲስ አበባ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነሮች አድርገው የሾሙት ባሳለፍነው ሳምንት ነው። ✍️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከልዑካቸው ጋር በጅቡቲ የቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሐመድ እና የጅቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ዑማር ጊሌ በተገኙበት ውይይት አድርገዋል። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥራ ጉብኝታቸውን ቀጥለውም ወደ ተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ያቀኑት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በዚሁ ወቅትም ከፕሬዚዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተወያይተዋል። ውይይታቸውም በሀገራቱ መካከል ለረጅም ዘመናት የቆየውን ወዳጅነት በማጎልበት፤ ትብብር እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር። ✍️ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ከዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ኅብረት ጋር መምከራቸው • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ባዘጋጀው የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይ ታድመዋል። በዚሁ ወቅትም የሁሉም እምነት፣ ባህልና ሥርዓት የሚከበርባት ኢትዮጵያን መገንባት የመደመር መንግሥት ተልዕኮ መሆኑን ገልጸዋል። • ከዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ኅብረት ዳይሬክተር ኮስማስ ዛቫዛቫ (ዶ/ር) ጋር በዲጂታል ልማት ያለ ትብብርን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት ያደረጉት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር። በቀጣይም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ከግብ ለማድረስ እና ትብብራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር በጀመርናቸው እና በሌሎች አዳዲስ ዘርፎች ዙሪያ በጋራ ለመሥራት ተስማምተናል ሲሉም ገልጸዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። • በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አዘጋጅነት በተከናወነው የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይም የታደሙ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት “ጎረቤቱ ርቦት እርሱ ጠግቦ የሚያድር ከኛ አይደለም” የሚለው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) አስተምኅሮ፣ ለሰው ልጅ ክብር መስጠትን፣ ርኅራኄን፣ የጋራ ደስታንና አብሮነትን በተግባር መተርጎም እንዳለብን የሚያሳይ ኅያው የሕይወት ስንቅ ነው ብለዋል። ✍️ የመሬት ናዳና ጎርፍ አደጋ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ • ባሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በተከሰተ የመሬት ናዳ እና ጎርፍ የዜጎች ሕይወት አልፏል፤ በንብረት ላይም ውድመት ደርሷል። ይህን ተከትሎም ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች የሐዘን መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል። • ከዚሁ ጋር በተያያዘ በጋሞ ዞን በመሬት ናዳ አደጋ የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም ከፌደራል መንግሥት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ከበደ ያስታወቁት ባሳለፍነው ሳምንት ነው። እስካሁንም በአደጋው ሳቢያ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስና መልሶ ለማቋቋም ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ በተቀናጀ መንገድ እየተሠራ መሆኑን አረጋግጠዋል። መላው የኢትዮጵያ ሕዝብም ለወገኑ ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ✍ ምክር ቤቱ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ማወጁ • የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት ምክንያት ሕይወታቸው ያለፉትን ዜጎች በማስመልከት ብሔራዊ የሐዘን ቀን ዐውጇል። በዚህም መሠረት ትናንት የጀመረው ብሔራዊ የሐዘን ቀኑ እስከ ነገ ድረስ የሚቆይ ይሆናል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ዐበይት_ጉዳዮች #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency
ኢትዮጵያ የገነነችበት ዲፕሎማሲና የስትራቴጂካዊ እይታ ስኬት!
Feb 25, 2026 435
(በሙሴ መለስ) ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ የሚደረጉ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች፣ ታላላቅ ዲፕሎማቶች ጉብኝቶች እና የግንኙነት መድረኮች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያላት ተሳትፎ እየጨመረ የዲፕሎማሲ ስኬቷም የተጽዕኖ ደረጃው እያደገ ስለመምጣቱ የሚያሳዩ ናቸው። የዓለም መሪዎች ከስትራቴጂካዊ አጋርነት እስከ ቀጣናዊ ትብብር የዘለቀ ግንኙነትን ዓላማ ያደረጉ ጉብኝቶችን በአፍሪካ መዲና ኢትዮጵያ አድርገዋል። ጉብኝቶቹ የኢትዮጵያን ጂኦ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ እና የዲፕሎማሲ አቅም የሚያሳዩም ናቸው። መሪዎቹ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ያደረጓቸው የሁለትዮሽ ውይይቶች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጎልበት እና በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ጥረቶች እንዲሁም የጋራ የሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በትብብር መፍታት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ የልብ ምት ናት። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ መሆኗ የዓለም መሪዎች ትኩረት እንዲያርፍባት አድርጓል። ጉብኝቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፈላጊነት ብቻ ሳይሆን ሰፊ በሆኑ ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ እያደገ ያለውን ተሰሚነቷን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። ፈተናዎች በበዙበት የአፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ በሰላም ግንባታ፣ ኢኮኖሚ ትብብር እና አህጉራዊ ትስስር ገንቢ ሚና እንደምትጫወት እና አስፈላጊነቷ ወሳኝ እንደሆነ ከመሪዎቹ ንግግር መረዳት ይቻላል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሃገራችንን ከጎበኙ የውጭ ሃገራት መሪዎች መካከል ባለፈው ሣምንት የመጡት የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን አንዱ ናቸው። ኤርዶዋን በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።ቱርኪዬ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እና አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትሻ ተናግረዋል። ኤርዶዋን ኢትዮጵያ በቀጣናው ስላላት ሚና በማንሳት ዓለም ፊቱን ወደ አፍሪካ ቀንድ ባዞረበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የሀገረ መንግስት መዋቅር እና ተምሳሌታዊ አስተዳደር የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱንም ተናግረዋል። ጉብኝቱ መልካም ውጤቶችን ይዞ እንደሚመጣና ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ሙሉ እምነት አለኝ ማለታቸውም አይዘነጋም። በዓለም ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር የያዘችው ህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ሞዲ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብስባ ላይ በመገኘት በጥልቅ ስሜት ባደረጉት ታሪካዊ ንግግርም ህንድ እና ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዳላቸው አንስተዋል። የህንድ ኩባንያዎች ለኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰው ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ በግብርና፣ ጨርቃ ጨርቅና ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራታቸውን አመልክተዋል። ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ስትራቴካዊ አጋርነት ምዕራፍ ለማሸጋገር መወሰኗን ገልጸው ይህም ኢኮኖሚ፣ ንግድ ፣ ኢንቨስመንት፣ ቴክኖሎጂ፣ ማዕድን፣ አረንጓዴ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ህንድን ታማኝ አጋር በማድረጓ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ናሬንድራ ሞዲ ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር አበክራ እንደምትሰራ መናገራቸው ሌላው የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያመለክት ሲሆን ሞዲ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ እና ዘመናዊ ህልሞችን አጣምራ መያዟ በአይበገሬነት እና በጽናት መንፈስ እንድትቀጥል አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም ጥንታዊ ስልጣኔዎች ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት መሆኗን ያነሱት የጥንካሬ፣ የአይበገሬነት፣ የኩራት እና የለውጥ ምልክት ናት ሲሉ መግለጻቸውም አይዘነጋም። በዚሁ ዓመት ታህሳስ ወር ላይ አዲስ አበባን የጎበኙት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን የልማት ስራዎች ያደነቁ ሲሆን ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በልማቱ ዘርፍ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሰራም አረጋግጠዋል። ቻይና ለቀጣናዊ ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እንደምትስራ በመግለጽም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት(all-weather strategic partnership) ይበልጥ ለማጎልበት በቁርጠኝነት ትሰራለች ብለዋል። የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳውና በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ዕዝ (አፍሪኮም) ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ያረጋገጡት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያን ቀጣናዊና ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ነበር። በወቅቱ ክርስቶፈር ላንዳው እና ልዑካቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን ዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኤክስፖም ጎብኝቷል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየውን አጋርነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን በመግለጽ አሜሪካ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት እንደምትፈልግም አመልክተዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያዊቷ ሀገር ሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ አዲስ አበባን የጎበኙት በህዳር ወር 2018 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደረጉ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ አዲስ አበባ በማድረጋቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሲንጋፖር በአዲስ አበባ ኤምባሲ ለመክፈት መወሰኗን በደስታ እንደተቀበሉት በወቅቱ ዎንግ ገልጸውም ነበር። የኤምባሲው መከፈት ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ህብረት እና ከመላው አፍሪካ ጋር ቁልፍ ትስስር መፍጠሪያ ሆኖ እንደሚያገለግልም አመልክተዋል። ሲንጋፖርና ኢትዮጵያ የየቀጣናቸው መግቢያ በር ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገራቱ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከር ዜጎችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርግ ድልድይ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና አፍሪካ መካከል እየገነቡ ነው ብለዋል። ከእስያ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስንመለስም የኬንያውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ባደረጉት ጉብኝት ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የመሪነት ሚና በማድነቅ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ገንቢ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ አንስተዋል።ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደምትሻም ገልጸዋል። በአውሮፓ የጠንካራ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆአን ዋድፑልም በጥር ወር ባደረጉት የኢትዮጵያ ጉብኝት ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የጀርመን ኩባንያዎች በግንባታው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ፣ ኮመንዌልዝ እና የልማት ጉዳዮች ሚኒስትር ይቬት ኩፐር፣ የኖርዌይ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪያስ ክራቪክ የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒትር ዴኤታ ኩኒሚትሱ አያኖ እና የሌሎች ሃገራት መሪዎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ የተደረጉ የከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች ጉብኝት ብቻ ሆነው ያለፉም ብቻ አይደሉም። ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያላትን ተሰሚነትም የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ እና ቱርኪዬን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ምዕራፍ አሸጋግረዋል። የዓለም ሀገራት መሪዎቹ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በመፍታት ረገድ ያላትን ወሳኝ ሚና አድንቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላት ስትራቴጂካዊ ሚናም የተነሳ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ የትብብር፣ የሰላም፣ የጋራ አጋርነት እና ዘላቂ ልማት ማዕከል መሆኗን የሚያሳይ ነው። ጉብኝቶቹ እንግዳን ተቀብሎ መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ከማድረግ ባለፈ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም የዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ቦታ አጉልተው ያመላከቱ የስኬት መገለጫዎችም ናቸው።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 3739
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 2512
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8304
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6789
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60674
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54619
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35173
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32771
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 27846
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 26999
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 26514
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26161
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 60674
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 54619
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 35173
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 32771
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ተከፍሎ የማያልቅ የኢትዮጵያ እና ሕዝቧ ውለታ አለብን - የመናዊያን ፍልሰተኞች
Mar 19, 2026 2318
በዮሐንስ ደርበው ምድረ ቀደምቷ ሀገር ኢትዮጵያ ለተገፉ፣ ጥላ ከለላ ለሚሹ፣ ለተከዙና ለታረዙ የሀገራት ዜጎች መጠጊያ ናት። የኢትዮጵያን ቸርነትም ከተጠለሉባት እንግዶቿ በላይ ምሥክር የለም። የኢትዮጵያን ደጅ የረገጡ ሁሉ በቆይታቸው ለተደረገላቸው ሁሉ ‘ውለታችንን በምን እንክፈል’ ሲሉ ይደመጣሉ። ከአያሌ ሀገራት በመልከ ብዙ ቀውሶች ሳቢያ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሁሉ የቆሰሉ ልባቸው ታክሞ፣ ዕንባቸው ታብሶና ሕይወታቸው ታድሶ ኑራቸውን አደላድለዋል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በዚህም ከአፍሪካም ሆነ ከተቀረው ክፍላተ ዓለም የጦርነትና ግጭት ጥላ ያጠላባቸውና ሰላምን የተጠሙ የቀጣናው ሀገራት ዜጎች ኢትዮጵያን ሲሹ ማየት የተለመደ ነው። የየመን ዜጎች ለዚህ ማሳያ ናቸው። ኢብቲሳም ኻሊድ እና መሰል የመናዊያን ከየመን የእርስ በርስ ግጭት በኋላ የኢትዮጵያን ደጅ ረግጠው ዛሬ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሚተርፍ የተድላ ኑሮ እየኖሩ ነው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረገችው ኢብቲሳም እንደምትለው፤ በየመን አለመረጋጋት በፈጠረው ጠባሳ እርሷና መሰሎቿ ለፍልሰት ተዳርገዋል። ለዚህ ደግሞ ምርጫቸው ኢትዮጵያ ሆነች። ወደ ኢትዮጵያም መጥተው የሀገሬው ፊት ሳይኮሰኩሳቸው በፍቅር እንደተቀበሏቸው ትናገራለች። በዚህም ዛሬ የመናዊያን ተስፋቸው ለምልሞ፣ ሕይወታቸው ሠምሮ ኢትዮጵያን እንደ እናት ቆጥረው እየኖሩ ስለመሆኑ ትናገራለች። ከ11 ዓመታት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የመጣችው ኢብቲሳም፤ በወቅቱ ቀኑ እንደጨለመባት ታወሳለች። ሰው ከቤቱ፣ ከወገኑ…ከሀገሩ ወጥቶ ወዴት ይሄዳል? በወቅቱ የነበረውን ጭንቀት ማየልም ታስታውሳለች። አሁን ግን ስለ ኢትዮጵያ እና ሕዝቧ በጎነት ዐውርታ አትጠግብም። “አሁን ፍልሰተኛ አይደለሁም፤ ያለሁት በሁለተኛዋ ሀገሬ ኢትዮጵያ ነውና” ትላለች። እንዲህ ባለው የረመዳን ወቅት ደግሞ የፍልሰተኞች ሁሉ ሰብሳቢ ናት። “ሁሉም ከእነ ቤተሰቡ ወደ ቤቷ እየመጣ ያፈጥራል። በዚህም በፍልሰት እንደመጡ ሳይሆን ቤተሰባዊነት ይሰማቸዋል። ከየመን፣ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ኤርትራ፣ አፍጋኒስታን፣ ኮንጎሊዝ (DRC) ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሁሉ ሰብሰብ ብለው የኢፍጣር መርሐ-ግብርን እንደሚያከናውኑም ታነሳለች። በዚህ ላይ ኢትዮጵያውያን ብርታት ናቸው ትላለች፤ ሁሌም ‘አይዟችሁ፣ በርቱ፣ ነገ ጥሩ ይሆናል’ እያሉ ያበረቱናል፤ ክብርና ፍቅር ይሰጡናል ስትልም ታስረዳለች። የኢትዮጵያንና ሕዝቧን ውለታ እንዴት መክፈል ይቻላል? ኢትዮጵያን ሀገራችን ብለን ነው እየጠራን ያለነው። እንደ እንግዳ እንደ ፍልሰተኛ እራሳችንን አናስብም፤ እንደሀገሬው አንዱ እንጅ፤ የምትለው ኢብቲሳም፤ ኢትዮጵያን እንዴት ብዬ ነው የምገልጻት? እናትን መግለጽ ይቻላል? እናትን መግለጽ ከተቻለ ኢትዮጵያን በዚያ ልክ መግለጽ ይቻል ይሆናል፤ እኔ ግን አይቻለኝም በማለት ትናገራለች። “የዛሬ 11 ዓመት ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት፤ የሰው ፊት አልገረፈኝም፤ ፊቱን ያዞረብኝም የለም። ኢትዮጵያውያን ደግ፣ ቅንና ደስ የምትሉ ሕዝቦች ናችሁ” ስትል ስሜቷን ትገልጻለች። ኢትዮጵያ እንደ ኒውዮርክ እያደገች ነው፤ እኛ ከመጣን በኋላ እንኳን በርካታ ለውጦች ዕያየን ነው ስትልም የኢትዮጵያን የለውጥ ሂደት አንስታለች። ለአብነትም ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በርካታ ነገሮች መስተካከላቸውን በመጠቆም፤ ለዚህም የኢትዮጵያን መንግሥት እናመሠግናለን ብላለች። ከፍልሰተኞች ጋር በተያያዘ በርካታ ሕጎች በመሻሻላቸው፤ ዛሬ በራሴ ስም ንግድ ፈቃድ አውጥቼ እየሠራሁ ነው፤ በጨረታዎችም እወዳደራለሁ፤ የበጎ አድራጎት ማኅበር መመሥረትና መምራት ችያለሁ። እነዚህ ሁሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ያመጣቸው ለውጦች ናቸው ብላለች። በምድረ ኢትዮጵያ ያለን ሁሉ ለኢትዮጵያ ዕድገት እንተባበር ስትልም ጥሪ አቅርባለች። ህልማችን ከኢትዮጵያውያን ጎን ሆነን ኢትዮጵያን በማሳደግ ጥረት በንቃት መሳተፍ ነው፤ የኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ውለታ መመለስ አለብን ስትልም ትናገራለች። በኢብቲሳም ኻሊድ ቤት በተዘጋጀ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ላይ የተሳተፈው አነስ አንዋር ለኢዜአ እንዳለው፤ ኢትዮጵያ በሯን ከፍታ አስጠልላዋለች። ከተለያዩ ሀገራት ብንመጣም ሰብሰብ ብለን ስናፈጥር፤ ማኅበራዊና ቤተሰባዊነታችን ይጠናክራል ብሏል። ብዙ ፈተናዎችን ዐይተናል፤ አልፈናቸው እዚህ ደርሰናል የሚለው አነስ፤ “ኢትዮጵያዊነት መልካምነት ነው” ሕዝቡ በክብር ነው የተቀበለን፤ ከምሥጋና ውጭ ምን ማለት እንችላለን? አመሥጋኞች ነን ሲል ገልጿል። እየተማርኩ ነው፤ ትምህርቴን አጠናቅቄ በሙያዬ በመሠማራት ኢትዮጵያን ማገዝ እፈልጋለሁ ብሏል። ራኪያ አሊ አብዱረዛቅ በበኩሏ በፈረንጆቹ 2011 ወደ ኢትዮጵያ መምጣቷን ታወሳለች። ትምህርቷንም ተከታትላ መመረቋን ገልጻ፤ ቤተሰብ አፍርታ ሁለት ልጆችንም ወልዳ እየኖረች ነው። ኢትዮጵያ ሁለተኛ ሀገሬ ናት፤ ሰላም አላት፤ ሕዝቡም ሰው አክባሪ ነው። ለኢትዮጵያ የተሻለ ልማት ደግሞ መተባበር ወሳኝ ስለሆነ ለዚሁ እንትጋ ስትል መልዕክቷን አስተላልፋለች። #ፍልሰተኞች #ኢዜአ
ከዛፍ የሚታለብ ወተት
Feb 27, 2026 653
በቀደሰ ተክሌ -(ከሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር ስትገናኝ ሌላ እውነት ሌላ አዲስ ነገር ትፈጥራለች። የሰው ልጅ የመመራመርና የማወቅ ተፈጥሯዊ ባህርይው በተፈጥሮ ላይ ሁሉን የማድረግ ሥልጣንን ያስቸረ ነው። ሰው ያልነበረን አዲስ ነገር መፍጠር ባይችልም፤ ከነበረው ሌላ ውጤት ማግኘት ወይም መፍጠር ይችላል። "ጉማታ" በረከትን የመጋራት እሴት!! በዓለማችን ሰውን እና እቃን ከቦታ ወደ ቦታ የማንቀሳቀስ ትልቅ አገልግሎት ያለው ተሽከርካሪ ሕይወት ያለው መስሎ እንዲታይ የሚያደርገው የተገጠመለት ጎማ ነው። ታዲያ ይህ ጎማ ከዛፍ በተገኘ የወተት ጠብታ የሚሰራ መሆኑ አግራሞትን ከሚፈጥሩ የጥበብ ሥራ ውጤቶች መካከል እንዲሆን ያደርገዋል። የጎማ መስሪያ የሆነው ጥሬ ምርት ከዛፍ እንዴት እንደሚዘጋጅ ከስፍራው ኢዜአ የተመለከተውን ሊያስቃኛችሁ እነሆ ይላል፡- በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጎማ ዛፍ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ይገኛል። በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የተባለው ይህ የጎማ ዛፍ ልማት በ3 ሺህ 884 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው። አረንጓዴ ካባ የደረበውን የበበቃ ቀዬ እንደተሻገሩ ቀጥ ቀጥ ብለው የቆሙ ዛፎች ቅርንጫፋቸውን ከመሬት ከፍ አድርገው ግንዱን ለሌላ ተግባር እየተዉ አድገው በአዲስ ብርሃን ቀበሌ ደምቀው ይታያሉ።   እነዚህ ዛፎች ከወገብ በታች ባለው ክፍል ብዙ ሺህ ጅራፍ እንዳረፈበት ገላ ሰምበር በሰንበር ሆነዋል። ይህም ሌሊት ሌሊት በሚፈጸም ከዛፉ ወተት ለማምረት በተደረገ ጥረት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ጎማን ለመሥራት የሚያስችለውና ከዛፉ የሚገኘውን ወተት ማምረትም የሰለጠኑ ባለሙያዎች ሌሊት ከ9 ሰዓት ጀምሮ የሚከውኑት ተግባር ነው። ይህን ሥራ ለማቀላጠፍም ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ላይና ታች ይላሉ። ሠራተኞቹም ራሳቸውን ከማስተዳደር ባለፈ በወዝ በላባቸው ለሀገር አዎንታዊ ተጠቃሚነት የሚውለውን ምርት ያቀርባሉ። የጎማ ዛፍ በተፈጥሮ ብዙ ወተት የሚይዘው ሌሊት ነው። ቀን የሰበሰበውን ወተት ሌሊት ያለ ስስት ይለግሳል። በዚህን ሰዓት ዛፉን አድምተው ወተት ሊያልቡ የተዘጋጁ ሠራተኞች በሰለጠኑት ሙያ መሠረት የፀሐይ መውጫና መግቢያ አቅጣጫን ቀድመው ይለያሉ። የፀሐዩን አቅጣጫ ከለዩ በኋላ በዛፉ ሰሜንና ደቡብ አቅጣጫ ጎን ላይ በስለታማ ቁስ በአንድ መስመር ቀጥ አድርገው በመፈቅፈቅ ለዛፉ ወተት መውረጃ ቦይ ያበጃሉ። በመቀጠል ሁለቱን መስመሮች ከፊት ለፊት የሚያገናኝ ሌላ መስመር በማበጀት የዛፉ ወተት መሰል ፈሳሽ ከስር ወደተቀመጠው ፈሳሽ መቀበያ ባልዲ ያለ ስስት ይፈሳል።   የጎማ ዛፍ ወተት ጠብታ ከእያንዳንዱ ዛፍ ስር ተሰብስቦ በብዙ ሊትር ተመዝኖ በበርሜል ይከማቻል። በአግባቡ የማጣራትና አሲድ ጨምሮ የማርጋት ሥራ ወደ ሚሰራበት ክፍል ይገባል። ወተቱ ከረጋ በኋላም ይታጠባል። ተድጦ የሚፈለገውን ያህል ቅርጽ ከያዘ በኋላ ጋቢ መስሎ ፀሐይ ላይ ይሰጣል።   በፀሐይ ኃይል ጠፈፍ እንዲል የተሰጣው ምርት የተያዘለት ሰዓት ሲጠናቀቅ በባህላዊ መንገድ ወደ ተዘጋጀው ጭስ ቤት ይላካል። በዚህ ክፍል ውስጥ ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ በተለያየ ደረጃ የተዘጋጁ እሳት ማንደጃ ጉድጓዶች ይገኛሉ። ከፀሐይ ላይ ተሰጥቶ ወደ ውስጥ እንዲገባ የተደረገው ምርት በዚህ ክፍል ከ5 እስከ 6 ቀናት የተለያዩ የድርቀት ደረጃዎችን እየተሸጋገረ ይቆያል። በጥሩ ሁኔታ ቀይ ሆኖ ከደረቀ በኋላ ለጎማ ኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ ሆኖ ለሽያጭ ዝግጁ ይሆናል።   ሁለት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረው የጎማ ልማትና ምርት ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የጎማ ጥሬ ዕቃ በከፊል በመሸፈን በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትና ምርት ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ እንደሚሉት፤ የጎማ ዛፍ አንድ ጊዜ ከተተከለ በኋላ ዓመቱን ሙሉ ምርት የሚሰጥ ዛፍ ነው። የወተት ምርት ለመስጠት ችግኙ ከተተከለ በኋላ ለሦስት ዓመታት ይቆያል።   በጉራፈርዳ ወረዳ ለምቶ ምርት እየሰጠ ካለው ዛፍ በወር ከ37 እስከ 40 ቶን የጎማ ዛፍ ጥሬ ምርት በመመረት ላይ ሲሆን ዘንድሮ ከ560 ቶን በላይ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ የዘርፉን የጥሬ ምርት ፍላጎት በከፊል ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ከ87 ሺህ ሄክታር በላይ ለጎማ ዛፍ ምቹ መሬት እንዳላት ጥናቶች ያመለክታሉ። ይሁን እንጂ በስፋት ወደዚህ ዘርፍ በመግባት የዘርፉን ኢኮኖሚ መጠቀም አልተቻለም። የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የጎማ ዛፍ ልማትን ለማስፋፋት አቅዶ በጥናት ከተለዩ ቦታዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቡር ዞን ከ2 ሺህ 500 ሔክታር በላይ መሬት ተረክቦ ችግኝ የማዘጋጀት ተግባር እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የሀገር ውስጥ የጥሬ ምርት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ በመሸፈን እና የተረፈውን ኤክስፖርት በማድረግ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚቻልበትን ዕድል ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን አቶ ዘማች ጠቁመዋል። ባለሃብቶች ወደዚህ ዘርፍ ቢሰማሩ ሀገርን የሚጠቅሙ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚቻልም አክለዋል። ኢትዮጵያ በየዘርፉ ያላት የኢኮኖሚ አቅም የዕድገት ጉዞዋ አቅሞች ናቸው። በተለይ ለም አፈሯ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶችን በማብቀል ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ሀብት መፍጠር የሚያስችሉ መሆናቸውን በብዙ መንገድ ማረጋገጥ እየተቻለ ነው። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የጎማ ዛፍ ልማትም ከእነዚህ አቅሞች አንዱ ነው። ያሉንን ጸጋዎች ለይቶ ለማልማትና ምርታማነትን ለመጨመር መንግሥት የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ የጎማ ዛፍ ምቹ አጋጣሚዎችን ለይቶ መሥራት ከተቻለ ከዘርፉ በብዙ መጠቀም ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም