ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የአዲስ አበባ ልማት ውጤቶች ለሰው ልጆች መኖሪያነት የሚገባን ክብር በተግባር የገለጡ ናቸው
Jul 19, 2026 31
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ውጤቶች ለሰው ልጆች መኖሪያነት የሚገባን ክብር በተግባር የገለጡ መሆናቸውን የክፍለ ከተማ ሥራ አስፈጻሚዎች ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሄድ የቆየውን የ2018 በጀት ዓመትና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በስኬት አጠናቋል። በበጀት ዓመቱም ከተማ አስተዳደሩ በጥቅሉ ከ96 በመቶ በላይ የአፈጻጸም ውጤት ማስመዝገብ እንደቻለ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በግምገማ መድረኩ፤ በበጀት ዓመቱ ለመፈጸም የተቀመጡ ግቦች አመርቂ ውጤት እንደተገኘባቸው አስረድተዋል። በግምገማው የተሳተፉት የአራዳና የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የመዲናዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በማሳደግ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስኬቶች ተመዝግበዋል። የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማቱም የመዲናዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ በመገንባት፣ ለነዋሪዎቿ ተገቢውን ክብር የምትሰጥ ከተማ እንድትሆን ማድረጉን ገልጸዋል።   የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወንድሙ ዑመር ፤ አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ክብር የሚሰጥ የከተማ ገጽታ በመላበስ፣ አስደማሚ የልማት ስኬቶች የሚመዘገቡባት ከተማ እየሆነች ነው ብለዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥና አዲስ የከተሜነት መኖሪያ ደረጃ ያሸጋገረ የልማት ባህል መፈጠሩን ገልጸዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኮሪደር፣ በወንዝ ዳርቻና በሰው-ተኮር የልማት መርሃ ግብሮች የተገኙ አመርቂ ውጤቶችም ነዋሪዎችን ከውስብስብ ችግሮች በማላቀቅ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።   የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታረቀኝ ወርቅነህ በበኩላቸው፤ አዲስ አበባ ውብና ማራኪ ገጽታን የተጎናጸፈች የአለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ማዕከል መሆኗን ገልጸዋል። በመዲናዋ የተገነቡ ጽዱ፣ ውብና ምቹ የልማት ስኬቶች፣ በተለይም የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርና ሌሎች ሰው-ተኮር ፕሮጀክቶች የዜጎችን ሕይወት በመቀየር ረገድ አመርቂ ውጤት ማስመዝገባቸውን አስረድተዋል።
ሁሉም ተቋማት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን የበለጠ በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ማስቀጠል ይጠበቅባቸዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 19, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሁሉም ተቋማት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን የበለጠ በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች "ትጋት ያሸልማል" በሚል መሪ ቃል የዕውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጀት ዓመቱ የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎችን በመሥራት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቢሮዎች፣ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ዕውቅናና ሽልማት አበርክተዋል። በዚሁ መሰረት የካቢኔ አባል ከሆኑና ከተሽከርካሪ ተሸላሚ ከሆኑ ቢሮዎች መካከል ሰላምና ጸጥታ፣ ጤና፣ ገቢዎች፣ ዲዛይንና ግንባታ እንዲሁም የትምህርት ቢሮዎች ይገኙበታል። የለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከልም ልዩ ሽልማት የተበረከተለት ሲሆን፤ በከተማ አስተዳደሩ የቦሌ፣ ለሚኩራና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች በተመሳሳይ የተሽከርካሪ ተሸላሚ ሆነዋል። የካቢኔ አባል ያልሆኑት የደንብ ማስከበር ባለስልጣን፣ የመንገዶች ባለስልጣን፣ የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን፣ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለስልጣን፣ እንዲሁም የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ተሸከርካሪ ተሸልመዋል። በተጨማሪም በሁሉም ክፍለ ከተማ ውስጥ ካሉ ወረዳዎች ከአንድ እስከ ሶስት የወጡ 33 ወረዳዎች ተሸላሚ ሲሆኑ፤ የፋይናንስ፣ የኢንዱስትሪ ልማት፣ የኮሙኒኬሽን፣ የንግድና ፍትሕ ቢሮዎችም የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።   ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት ፤ በ2018 በጀት ዓመት በተያዙ ዕቅዶች መሰረት ከ96 በመቶ በላይ የአፈጻጸም ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ መዋቅሮች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና በሌሎች መስኮች ላስመዘገቡት ውጤታማ የልማት አፈጻጸሞች ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም ሁሉም ተቋማት የተገኙ ስኬቶችን የበለጠ በማሳደግና ክፍተቶችን በመሙላት ለተሻለ የልማት ስኬት ገንቢ ሚና መጫወት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው፤ ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ ታላላቅ ኮንፈረንሶች፣ ህዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት በስኬት እንዲከበሩ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።   ተቋማቸው የተሸለመው በኤሌክትሪክ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለቀጣይ ሥራ ትልቅ ኃላፊነት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በበኩላቸው፤ የተበረከተላቸው የኤሌክትሪክ መኪና ሽልማት በጤናው ዘርፍ ለተመዘገበው ስኬታማ አፈጻጸም የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን ገልጸዋል።   በከተማው 68 የጤና ተቋማት የመረጃ አያያዝን ወረቀት-አልባ በማድረጋቸው እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን አስረድተዋል። የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አደፍርስ ኮራ በበኩላቸው፤ በክፍለ ከተማዋ የመዲናዋን ውብ ገጽታ የሚያላብሱ ስኬታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።   ክፍለ ከተማው የተሰጠው ሽልማትም የልማት አጋሮችን በማስተባበር በኮሪደር፣ በመንገድ፣ በወጣቶች መዝናኛና ስፖርት ማዘውተሪያ ላይ ላስመዘገበው የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን ተናግረዋል።
ጨፌ ኦሮሚያ ለክልሉ መንግሥት የ2019 በጀት ዓመት ሥራ ማስፈጸሚያ 704 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ
Jul 19, 2026 37
አዳማ፣ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ጨፌ ኦሮሚያ ለተያዘው በጀት ዓመት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል 704 ቢሊዮን ብር በጀት በሙሉ ድምፅ አጸደቀ። ጨፌ ኦሮሚያ በ6ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤው የዛሬ ውሎ የክልሉን መንግሥት የ2019 በጀት አጽድቋል። የኦሮሚያ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶሎሳ ገደፋ የበጀት ዝርዝሩን ለጨፌው ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በጀቱ ከተረጂነት ለመውጣትና ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብና ስትራቴጂ ለማሳካት ያለመ ነው። የበጀት ድልድሉም የልማት ፕሮግራሞችን መሠረት በማድረግና የክልሉን ዕድገት ለማፋጠን በሚያስችል መልኩ ተከናውኗል ብለዋል። የልማት ዕቅዱን ውጤታማ ለማድረግ ከሁሉም የክልሉ ሴክተር ተቋማት ጋር ውይይት መደረጉን የጠቀሱት ኃላፊው፤ ትኩረት ለሚሹ ጉዳዮች በበጀት ድልድሉ ቅድሚያ መሰጠቱን ተናግረዋል።   በጀቱ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ76 በመቶ ጭማሪ ያለው ሲሆን፣ የበጀት ድልድሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ በተለይም በከተሞችና በወረዳዎች ለሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል ብለዋል። በዚህም መሠረት ለጤና፣ ለትምህርት እና ለመንገድ መሠረተ ልማት አንዲሁም ለመስኖ እና ለንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ቅድሚያ ተሰጥቷል ነው ያሉት። ይህ በጀት በከተሞችና በወረዳዎች መካከል ሊኖር የሚችለውን የመሠረተ ልማት ልዩነት ለማጥበብና በክልሉ ቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ሰፋፊ መሬቶችን ለማልማት የሚያስችሉ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ታሳቢ ማድረጉንም ኃላፊው ገልጸዋል። ከተሞችና ወረዳዎች የሚሰጣቸውን በጀት ለማኅበራዊ መሠረተ ልማት ማዋል ላይ ትኩረት አድርገው መደልደል እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ማንኛውንም የገቢ ዓይነት ያለ ሕጋዊ ደረሰኝ መሰብሰብ የተከለከለና የሕግ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑንም አሳስበዋል። የጨፌው አባላት በቀረበው የበጀት ቀመር ላይ በሰጡት አስተያየት፤ የበጀት ድልድሉ ከተረጂነት ለመውጣትና ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ከበጀት ድልድሉ ባለፈ፣ የካፒታል በጀትን ጨምሮ የተመደበው ሀብት ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን የመደጋገፍ ባህል እያጎለበተ ነው
Jul 19, 2026 44
ጅግጅጋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን የእርስ በርስ መደጋገፍና ግንኙነት እያጎለበተ መምጣቱን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ገለጸ። "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የዘንድሮ ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊዎች በሶማሌ ክልል የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራትን አከናውነዋል። ወጣቶቹ በጅግጅጋ ከተማ ደም ከመለገስ ባለፈ የአቅመ ደካማ ወገኖችን መኖሪያ ቤቶች የመገንባት መርሐግብር አከናውነዋል። በመርሀግብሩ ላይ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የበጎፈቃድ ከፍተኛ ባለሙያ እና የቡድኑ አስተባባሪ እንደገና ፍቃዱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በእርስ ግንኙነት የሚጠናከርበትና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች የሚከናወኑበት ነው።   ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች ሀገር መሆኗን አስታውሰው፣ ወጣቶቹ ለአንድ ዓላማ መሰባሰባቸው ግንኙነታቸውን ከማጠናከር ባለፈ በሚደርሱባቸው አካባቢዎች የባህል ልውውጥ ለማድረግ ያስችላቸዋል ብለዋል። የሚሰጡት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትም የህብረተሰቡን ማህበራዊ ችግር በማቃለል አብሮነትን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ነው የገለጹት። በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከሀገሪቱ ሁሉም ክልሎች የተውጣጡ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች በማከናወን ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል። በዚህም በተለይ በአካባቢ ጥበቃ፣ አቅመ ደካማ ወገኖችን በተለያየ መንገድ በመደገፍ እንዲሁም በትምህርት፣ በጤና እና በተለያዩ የልማት ዘርፎች በመሰማራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የትግራይ ሕዝብ ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በትክክል ያንጸባረቀ ስኬታማ ሰልፍ ተካሂዷል 
Jul 19, 2026 76
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የትግራይ ሕዝብ ድምጹን ያሰማበትና ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በትክክል ያንጸባረቀ ውጤታማ ሰልፍ መካሄዱን የትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት ገለጸ። በትግራይ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን አፈና እና ጭቆና የሚያወግዝ እንዲሁም የጦርነት ዝግጅትን የሚቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ትናንት በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ተካሄዷል። በትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት "አፈሳ ይቁም፣ ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ ሐሳብ በተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በአዲስ አበባና በአካባቢው የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች፣ የሲቪክ ማህበራትና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። ሰልፉን በተመለከተ የትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት መግለጫ ሰጥቷል። የምክር ቤቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አሰፋ ሰልፉን በተመለከተ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ የትግራይ ተወላጆችና ሌሎች የከተማዋ ነዋሪዎች በነቂስ በመውጣት ድምፃቸውን አሰምተዋል። ሰላማዊ ሰልፉ የተለያዩ ዓላማዎችን አንግቦ የተካሄደ ሲሆን፤ ስኬታማ ሆኖ መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ እየፈጸመ ያለው ድርጊት የትግራይን ሕዝብ በእጅጉ እንዳሳሰበው ገልጸው፤ ሰልፉ ስምምነቱ በአስቸኳይ እንዲተገበር የተጠየቀበት መሆኑን ተናግረዋል። ወጣቶች ወደ ጦርነት እንዲገቡ እየተደረገ ያለው አስገዳጅ አፈሳ ወንጀል መሆኑን የገለጹት የምክር ቤቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ፤ ይህንም ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የማሳወቅና ድርጊቱ በአስቸኳይ እንዲቆም መልዕክት የተላለፈበት ሰልፍ እንደነበር አብራርተዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን እያደረገ ያለውን የጦርነት ዝግጅት እንዲያቆም የትግራይ ሕዝብ ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ሰልፍ መሆኑንም ተናግረዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የሕዝቡን ተቃውሞ ለመመከት መድረኮችን እየጠራ በኃይል ለማስፈራራትና ለማስገደድ መሞከሩን ጠቁመው፤ ሕዝቡ ግን ለሰልፉ ያለውን ድጋፍ ቤቱ በመቀመጥ በተግባር አሳይቷል ብለዋል። ሕዝቡ ትግራይን ድጋሚ ወደ ጦርነት ለመክተት እየተደረገ ያለውን ጥረት አጥብቆ እየተቃወመ እንደሚገኝም አመልክተዋል። የትግራይን ሰቆቃ ለማስቀረት የምንሰራውን ሥራ እናጠናክራለን ያሉት ኃላፊው፤ለዚህም ሁሉም በጋራ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል። ሰልፉ እንዲሳካ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበው፣ መሰል የሕዝብ ድምፅ ማሰሚያ ሰልፎች በሌሎችም አካባቢዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።
የሚታይ
የአዲስ አበባ ልማት ውጤቶች ለሰው ልጆች መኖሪያነት የሚገባን ክብር በተግባር የገለጡ ናቸው
Jul 19, 2026 31
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ውጤቶች ለሰው ልጆች መኖሪያነት የሚገባን ክብር በተግባር የገለጡ መሆናቸውን የክፍለ ከተማ ሥራ አስፈጻሚዎች ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሄድ የቆየውን የ2018 በጀት ዓመትና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በስኬት አጠናቋል። በበጀት ዓመቱም ከተማ አስተዳደሩ በጥቅሉ ከ96 በመቶ በላይ የአፈጻጸም ውጤት ማስመዝገብ እንደቻለ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በግምገማ መድረኩ፤ በበጀት ዓመቱ ለመፈጸም የተቀመጡ ግቦች አመርቂ ውጤት እንደተገኘባቸው አስረድተዋል። በግምገማው የተሳተፉት የአራዳና የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የመዲናዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በማሳደግ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስኬቶች ተመዝግበዋል። የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማቱም የመዲናዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ በመገንባት፣ ለነዋሪዎቿ ተገቢውን ክብር የምትሰጥ ከተማ እንድትሆን ማድረጉን ገልጸዋል።   የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወንድሙ ዑመር ፤ አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ክብር የሚሰጥ የከተማ ገጽታ በመላበስ፣ አስደማሚ የልማት ስኬቶች የሚመዘገቡባት ከተማ እየሆነች ነው ብለዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥና አዲስ የከተሜነት መኖሪያ ደረጃ ያሸጋገረ የልማት ባህል መፈጠሩን ገልጸዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኮሪደር፣ በወንዝ ዳርቻና በሰው-ተኮር የልማት መርሃ ግብሮች የተገኙ አመርቂ ውጤቶችም ነዋሪዎችን ከውስብስብ ችግሮች በማላቀቅ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።   የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታረቀኝ ወርቅነህ በበኩላቸው፤ አዲስ አበባ ውብና ማራኪ ገጽታን የተጎናጸፈች የአለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ማዕከል መሆኗን ገልጸዋል። በመዲናዋ የተገነቡ ጽዱ፣ ውብና ምቹ የልማት ስኬቶች፣ በተለይም የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርና ሌሎች ሰው-ተኮር ፕሮጀክቶች የዜጎችን ሕይወት በመቀየር ረገድ አመርቂ ውጤት ማስመዝገባቸውን አስረድተዋል።
ሁሉም ተቋማት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን የበለጠ በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ማስቀጠል ይጠበቅባቸዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 19, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሁሉም ተቋማት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን የበለጠ በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች "ትጋት ያሸልማል" በሚል መሪ ቃል የዕውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጀት ዓመቱ የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎችን በመሥራት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቢሮዎች፣ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ዕውቅናና ሽልማት አበርክተዋል። በዚሁ መሰረት የካቢኔ አባል ከሆኑና ከተሽከርካሪ ተሸላሚ ከሆኑ ቢሮዎች መካከል ሰላምና ጸጥታ፣ ጤና፣ ገቢዎች፣ ዲዛይንና ግንባታ እንዲሁም የትምህርት ቢሮዎች ይገኙበታል። የለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከልም ልዩ ሽልማት የተበረከተለት ሲሆን፤ በከተማ አስተዳደሩ የቦሌ፣ ለሚኩራና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች በተመሳሳይ የተሽከርካሪ ተሸላሚ ሆነዋል። የካቢኔ አባል ያልሆኑት የደንብ ማስከበር ባለስልጣን፣ የመንገዶች ባለስልጣን፣ የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን፣ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለስልጣን፣ እንዲሁም የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ተሸከርካሪ ተሸልመዋል። በተጨማሪም በሁሉም ክፍለ ከተማ ውስጥ ካሉ ወረዳዎች ከአንድ እስከ ሶስት የወጡ 33 ወረዳዎች ተሸላሚ ሲሆኑ፤ የፋይናንስ፣ የኢንዱስትሪ ልማት፣ የኮሙኒኬሽን፣ የንግድና ፍትሕ ቢሮዎችም የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።   ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት ፤ በ2018 በጀት ዓመት በተያዙ ዕቅዶች መሰረት ከ96 በመቶ በላይ የአፈጻጸም ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ መዋቅሮች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና በሌሎች መስኮች ላስመዘገቡት ውጤታማ የልማት አፈጻጸሞች ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም ሁሉም ተቋማት የተገኙ ስኬቶችን የበለጠ በማሳደግና ክፍተቶችን በመሙላት ለተሻለ የልማት ስኬት ገንቢ ሚና መጫወት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው፤ ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ ታላላቅ ኮንፈረንሶች፣ ህዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት በስኬት እንዲከበሩ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።   ተቋማቸው የተሸለመው በኤሌክትሪክ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለቀጣይ ሥራ ትልቅ ኃላፊነት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በበኩላቸው፤ የተበረከተላቸው የኤሌክትሪክ መኪና ሽልማት በጤናው ዘርፍ ለተመዘገበው ስኬታማ አፈጻጸም የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን ገልጸዋል።   በከተማው 68 የጤና ተቋማት የመረጃ አያያዝን ወረቀት-አልባ በማድረጋቸው እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን አስረድተዋል። የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አደፍርስ ኮራ በበኩላቸው፤ በክፍለ ከተማዋ የመዲናዋን ውብ ገጽታ የሚያላብሱ ስኬታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።   ክፍለ ከተማው የተሰጠው ሽልማትም የልማት አጋሮችን በማስተባበር በኮሪደር፣ በመንገድ፣ በወጣቶች መዝናኛና ስፖርት ማዘውተሪያ ላይ ላስመዘገበው የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን ተናግረዋል።
የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሕዝብና መንግሥትን መተማመን እያጎለበተ ነው 
Jul 19, 2026 79
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለው መተማመን እንዲጎለብት ማድረጉን የአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ደሳለኝ ተረፈ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የ2018 በጀት ዓመት እና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈፃጸም ግምገማ በስኬት አጠናቋል። በዚሁ መድረክ ላይ ከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ በጥቅሉ ከ96 በመቶ በላይ የሚሆን የአፈፃጸም ስኬት ማስመዝገብ እንደቻለ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ መድረኩ በበጀት ዓመቱ ለመፈጸም የተቀመጡ ታላላቅ ግቦች እንዲሁም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ስትራቴጂክ ዕቅዶች ምን ያህል ውጤታማ በሆነ መንገድ እንደተከናወኑ በጥልቀት የተገመገመበት መሆኑን ገልጸዋል። የአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ደሳለኝ ተረፈ፤ ቀደም ሲል ከፍተኛ ስብራት የነበረበትን የአገልግሎት ዘርፍ ለማሻሻል እና የህዝቡን እርካታ ለማረጋገጥ ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከተማ አስተዳደሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ የተጀመረው ዘመናዊው የአዲስ መሶብ ዲጂታል አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ 11 ቋሚ ቦታዎች እና አንድ ተንቀሳቃሽ ማዕከል ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የ 25 ተቋማትን 150 የተለያዩ አገልግሎቶች በአንድ ጣራ ስር በማስተናገድ ላይ የሚገኘው ይህ ስኬታማ የዲጂታል ሽግግር ፕሮጀክት፣ በቀጣይም ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋፋት በልዩ ትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ አብራርተዋል። የአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመር የህብረተሰቡን የዘመናት ምሬት በዘላቂነት የፈታ ሲሆን፣ በአገልግሎቱም የህዝቡን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ተችሏል። ይህ ዘመናዊ አሰራር ህዝቡ የሚፈልገውን አገልግሎት በአንድ ማዕከል በቀላሉ እንዲያገኝ በማድረግ በመንግስትና በህብረተሰቡ መካከል ያለውን የጋራ መተማመን ይበልጥ ማጎልበት መቻሉን ገልጸዋል።
በመዲናዋ የመኖሪያ ቤት ፍላጎትና አቅርቦትን የሚያቀራርብ አማራጭ የቤት ልማት መርሃ ግብር እየተከናወነ ነው
Jul 19, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የመኖሪያ ቤት ፍላጎትና አቅርቦቱን የሚያቀራርብ ስኬታማ የብዝኅ ቤት ልማት አማራጭ መርሃ ግብር እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሄድ የቆየውን የ2018 በጀት ዓመት እና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በስኬት አጠናቋል። በበጀት ዓመቱም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጥቅሉ ከ96 በመቶ በላይ የአፈጻጸም ውጤት ማስመዝገብ እንደቻለ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በግምገማ መድረኩ ፤ በበጀት ዓመቱ ለመፈጸም የተቀመጡ ግቦች አመርቂ ውጤት እንደተገኘባቸው አስረድተዋል። በግምገማው የተሳተፉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በቤት ልማት ዘርፍ ውጤታማ ሥራዎች ተሰርተዋል። ለአብነትም በመንግሥት፣ በግልና መንግሥት አጋርነት እንዲሁም በግል ባለሃብቶች ብዝኅ የቤት ልማት አማራጭ መርሃ ግብር የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ፍላጎትና አቅርቦት የሚያቀራርብ ስኬታማ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህ ጥረትም ከዚህ ቀደም የነበረውን የቤት አቅርቦት እጥረት በመቅረፍ በመደመር እይታ አመርቂ የቤት ልማት ውጤት ማምጣት እየተቻለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በ2018 በጀት ዓመት በመንግሥት በጀት ብቻ ግንባታቸው የተጠናቀቁና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ 50 ሺህ 305 ቤቶች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዳሴው ግድብ ምርቃት ወቅት ባበሰሩት የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶች ግንባታ መርሃ ግብር፤ የመኖሪያ ቤት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ማስገንዘባቸው ይታወሳል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተቋማት ዕውቅና ሰጡ
Jul 19, 2026 86
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 12/ 2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ2018 በጀት ዓመት የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎችን በመሥራት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቢሮዎች፣ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች ዕውቅናና ሽልማት አበርክተዋል።   በዚሁም መሰረት፦ የካቢኔ አባል ከሆኑ ቢሮዎች፦(መኪና ተሸላሚዎች) 1ኛ. ሰላምና ፀጥታ ቢሮ 2ኛ. ጤና ቢሮ 3ኛ. ገቢዎች ቢሮ እና ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ 4ኛ. ትምህርት ቢሮ 5ኛ. ልዩ ተሸላሚ የሆነው :-ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ከክፍለ ከተሞች፦ (መኪና ተሸላሚዎች) 1ኛ. ቦሌ ክፍለ ከተማ 2ኛ. ለሚኩራ ክፍለ ከተማ 3ኛ. አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የካቢኔ አባል ካልሆኑ ተቋማት፦ (መኪና ተሸላሚዎች) 1ኛ. ደንብ ማስከበር ባለስልጣን 2ኛ. መንገዶች ባለስልጣን 3ኛ. ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን 4ኛ. አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለስልጣን 5ኛ. ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ሲሆን በተጨማሪም 33 ወረዳዎች፣ ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከእያንዳንዱ ወረዳ ከአንድ እስከ ሶስት የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ተሸላሚ ሆነዋል። የካቢኔ አባል ከሆኑ ቢሮዎች፦የሰርተፍኬት ተሸላሚዎች 1. ፋይናንስ ቢሮ 2. ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ 3. ኮሙኒኬሽን ቢሮ 4. ንግድ ቢሮና 5. ፍትሕ ቢሮ የካቢኔ አባል ካልሆኑ ተቋማት፦(የሰርተፍኬት ተሸላሚዎች) 1. ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት 2. የመስሪያ ቦታዎች ልማት አስተዳደር 3. አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ከክፍለ ከተሞች:- (የሰርተፍኬት ተሸላሚዎች) 1. ኮልፌ ክፍለ ከተማ 2. ልደታ ክፍለ ከተማና የካ ክፍለ ከተማ ናቸው።   ዛሬ የተሰጠነው እውቅናና ሽልማት የሁሉም አመራር፣ በየደረጃው ያሉ ባለሞያዎች፣ የባለድርሻ አካላት እና አብሮን ለሰራው ህዝባችን ለጋራ የቅንጅት ስራ የተሰጠ ሲሆን ይህም ይበልጥ ሰርተን የህዝባችንን የመልማት ፍላጎት የምናሳካበት፣ የውድድር መንፈስን የምንፈጥርበት፣ ወደኋላ የቀሩት ራሳቸውን ፈትሸው ወደፊት የሚመጡበት እንጂ የሚያዘናጋን አይደለም ነው ያሉት። በመሆኑም፤ እውቅናው በቀጣይ በጀት ዓመት አልቀን በመስራት የህዝባችንን ተጠቃሚነት እንድናረጋግጥ፣ የአገልግሎት ተደራሽነትን አልቀን እንድንሰራ ከትልቅ አደራም ጭምር ነው ብለዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
የትግራይ ሕዝብ ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በትክክል ያንጸባረቀ ስኬታማ ሰልፍ ተካሂዷል 
Jul 19, 2026 76
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የትግራይ ሕዝብ ድምጹን ያሰማበትና ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በትክክል ያንጸባረቀ ውጤታማ ሰልፍ መካሄዱን የትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት ገለጸ። በትግራይ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን አፈና እና ጭቆና የሚያወግዝ እንዲሁም የጦርነት ዝግጅትን የሚቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ትናንት በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ተካሄዷል። በትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት "አፈሳ ይቁም፣ ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ ሐሳብ በተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በአዲስ አበባና በአካባቢው የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች፣ የሲቪክ ማህበራትና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። ሰልፉን በተመለከተ የትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት መግለጫ ሰጥቷል። የምክር ቤቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አሰፋ ሰልፉን በተመለከተ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ የትግራይ ተወላጆችና ሌሎች የከተማዋ ነዋሪዎች በነቂስ በመውጣት ድምፃቸውን አሰምተዋል። ሰላማዊ ሰልፉ የተለያዩ ዓላማዎችን አንግቦ የተካሄደ ሲሆን፤ ስኬታማ ሆኖ መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ እየፈጸመ ያለው ድርጊት የትግራይን ሕዝብ በእጅጉ እንዳሳሰበው ገልጸው፤ ሰልፉ ስምምነቱ በአስቸኳይ እንዲተገበር የተጠየቀበት መሆኑን ተናግረዋል። ወጣቶች ወደ ጦርነት እንዲገቡ እየተደረገ ያለው አስገዳጅ አፈሳ ወንጀል መሆኑን የገለጹት የምክር ቤቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ፤ ይህንም ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የማሳወቅና ድርጊቱ በአስቸኳይ እንዲቆም መልዕክት የተላለፈበት ሰልፍ እንደነበር አብራርተዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን እያደረገ ያለውን የጦርነት ዝግጅት እንዲያቆም የትግራይ ሕዝብ ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ሰልፍ መሆኑንም ተናግረዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የሕዝቡን ተቃውሞ ለመመከት መድረኮችን እየጠራ በኃይል ለማስፈራራትና ለማስገደድ መሞከሩን ጠቁመው፤ ሕዝቡ ግን ለሰልፉ ያለውን ድጋፍ ቤቱ በመቀመጥ በተግባር አሳይቷል ብለዋል። ሕዝቡ ትግራይን ድጋሚ ወደ ጦርነት ለመክተት እየተደረገ ያለውን ጥረት አጥብቆ እየተቃወመ እንደሚገኝም አመልክተዋል። የትግራይን ሰቆቃ ለማስቀረት የምንሰራውን ሥራ እናጠናክራለን ያሉት ኃላፊው፤ለዚህም ሁሉም በጋራ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል። ሰልፉ እንዲሳካ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበው፣ መሰል የሕዝብ ድምፅ ማሰሚያ ሰልፎች በሌሎችም አካባቢዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።
ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለመላው ኢትዮጵያዊያን የተላለፈ መልዕክት
Jul 19, 2026 161
በሀገራችን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከናወነ ያለውና ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ የሚመካከሩበት ታሪካዊ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ እንዲሳካ ዜጎች ራሳቸውን ከሀሰተኛ መረጃ በመጠበቅ እና በኮሚሽኑ ላይ ሙሉ እምነት በማሳደር ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥሪ ያቀርባል፡፡ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረውን ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በተመለከተ አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች በማህበራዊ ሚዲያ አውታሮች አማካኝነት ከእውነታ የራቁ መረጃዎችን እያሰራጩ መሆኑን ኮሚሽኑ ደርሶበታል፡፡ ኮሚሽኑ የመናገር ነጻነትን ሙሉ በሙሉ የሚያከብር ገለልተኛ ተቋም እንደመሆኑ ገንቢ የሆኑ ሃሳቦችንና ውይይቶችን የሚቀበል ቢሆንም ሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ በሀሰተኛ መረጃዎች እንዳይታለል አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ ለህዝብ ይፋ ለማድረግ ይገደዳል፡፡ ሀገራዊ ምክክሩ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ነው። የዚህ ሂደት ስኬት የሚወሰነው ዜጎች በትዕግስት፣ በጥበብ እና በጋራ የኃላፊነት ስሜት ለመሳተፍ በሚያሳዩት የጋራ ቁርጠኝነት ላይ ነው። ይህም እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ሂደቱ ተጀመረ እንጂ ውጤቱ ገና ነው፡፡ ይህንን ውጤት በትዕግስት መጠበቅ ደግሞ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚጠበቅ ይሆናል፡፡ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ኮሚሽኑ ባወጣቸው የአሰራር ሂደቶች መሰረት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በዚህ መሰረት ባለፉት አራት ቀናት ኮሚሽኑ የጉባኤው ተሳታፊዎች የተጣለባቸውን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ ማድረግን ጨምሮ ለሂደቱ ጠቃሚ በሆኑ የእውቀት እና የስነ-ልቦና ዝግጅቶች እንዲያደርጉ መደላድሉን ፈጥሯል፤ ይህም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው አንድ አካል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ይህ እየሆነ ባለበት አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ኮሚሽኑ ምክክሩን ለመጀመር እክል እንደገጠመው የተሳሳተ መረጃ ሲያሰራጩ ተመልክተናል፡፡ በመሆኑም መሰል የተሳሳቱ መረጃዎች የራሳቸው ዓላማ ባላቸው ግለሰቦችና ቡድኖች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ስለሚችሉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በየእለቱ የሚኖሩ የምክክር ሂደቶችን ኮሚሽኑ ከሚሰጣቸው መግለጫዎችና የምክክሩን ሂደት ለመዘገብ በስፍራው ከተገኙ መገናኛ ብዙኃን ብቻ በመከታተል ራሱን ከተሳሳቱ መረጃዎች በመጠበቅ የምክክሩን ሂደት እንዲደግፍ ኮሚሽኑ ጥሪ ያቀርባል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም
ጽኑ ሰላምና ልማት እንጂ የሕገ-ወጡን የሕወሓት ቡድን የጦርነት ዳንኪራ አንፈልግም
Jul 19, 2026 122
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል ወጣትና ህዝብ ጽኑ ሰላምና ልማት እንጂ የሕገ-ወጡን የሕወሓት ቡድን የጦርነት ዳንኪራ እንደማይፈልግ የሕገ-ወጡን ቡድን አፈሳና አፈና ሸሽተው አዲስ አበባ የመጡ ወጣቶች ገለጹ። በትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት አስተባባሪነት ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን አፈሳና አፈና በመቃወም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል። ''አፈሳ ይቁም፤ ሰላም ይስፈን'' በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ የክልሉ ተወላጆች፣ ግፍን በመሸሽ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ወጣቶች፣ የሲቪክ ማህበራትና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። አፈሳና አፈናውን በመሸሽ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ወጣቶች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የክልሉን ወጣቶች በግዳጅ በማፈስ ወደ ጦር ካምፖች እያጋዛቸው ይገኛል። ሕገ-ወጥ ቡድኑም የክልሉን ወጣቶች ለሱዳንና ሻቢያ የጥፋት ኃይሎች በመሸጥ ሰብዓዊ ክብርን የሚጋፋ ኢ-ሰብዓዊ ግፍ እየፈጸመ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወጣት ሶሎሞን እምባዬ፤ ጦርነት ናፋቂው ሕገ-ወጥ ቡድን ካለፈው ስህተቱ ሳይማር ለዳግም ጦርነት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ ገልጿል። የጦርነት ነጋዴው ሕገ-ወጥ ቡድን ፅምዶ በተሰኘ የጥፋት ጥምረት ወጣቶችን በየቤተ-ዕምነቱ፣ በገበያና በየመንገዱ ለቅሞ በመውሰድና ለውጭ ገበያ ጭምር በመሸጥ እናቶችን እያስለቀሰ መሆኑን ተናግሯል። የትግራይ ሕዝብ ፍላጎት ጽኑ ሰላምና ልማት ብቻ መሆኑን ያነሳው ወጣቱ፤ እናቶችም የጦር መሳሪያ ካነገበው ኃይል ጋር በመጋፈጥ ተቃውሟቸውን እያሰሙ መሆናቸውን አክሏል። ፌዴራል መንግሥትም የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በማፍረስ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን ከፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በፈጠረው የጥፋት ጥምረት በሕዝቡ ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና መከራ እንዲያስቆም ጥሪ አቅርቧል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወጣት እምሩ ብርሃኑ በበኩሉ፤ ሕገ-ወጡ ቡድን ወጣቶችን ለውጭ ኃይሎች በመሸጥ የገቢ ምንጭ ማድረጉ የአደባባይ ምስጢር ከሆነ መሰነባበቱን ገልጿል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ወጣቶችና ሕዝብም የቡድኑን የጦርነት ጉሰማ በመታገል ሰላም ፈላጊነታቸውን በተግባር ሊያሳዩ እንደሚገባ አሳስቧል። ወጣት መብራህቱ ኻልአዩ በበኩሉ፤ ቡድኑ በክልሉ የከፈተው የአፈሳና የአፈና ጭቆና ሕዝብን ለስቃይ፣ ወጣቶችን ደግሞ ለስደት መዳረጉን ጠቁሟል። አክሎም ቡድኑ ወጣቶችን በማፈን ከሚፈፅመው ግፍ በተጨማሪም አርሶ አደሩ የእርሻ ሥራውን በአግባቡ እንዳያከናውን ተጽዕኖ እየፈጠረ መሆኑን ተናግሯል።
በክልሉ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማስተባበር በተሰራው ሥራ ውጤት ተገኝቷል
Jul 19, 2026 179
ቦንጋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በክልሉ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማስተባበር በተሰራው ሥራ ውጤት መገኘቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። የክልሉ የፓርቲና መንግስት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡   መድረኩን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ የአመራሩን የመፈጸም አቅም በማቀናጀት በበጀት ዓመቱ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ፣ በመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥም ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማስተባበር በተሰራው ሥራ ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል። የግብርናውን ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ባለፈ የኩታ ገጠም አሰራርን በመተግበር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ጥረት መደረጉንም አንስተዋል፡፡ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የሻይና ቡና ልማትን ለማሳካት በርብርብ መሰራቱን አስታወሰው፤ በበጀት ዓመቱ 61 ሺህ ቶን የታጠበና ያልታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡንም ኢንጂነር ነጋሽ (ዶ/ር) ገልፀዋል።   የማዕድል ልማትን በተገቢው በመምራትም 348 ኪ.ግ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደተቻለ ጠቅሰው፣ የክልሉን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ በተደረገ ሰፊ ርብርብም ከ18 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ተናግረዋል። በመድረኩ በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት እና የክልሉ መንግስት የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2019 በጀት የዓመት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል። በመድረኩ የክልሉ፣ የዞኖች እና የከተማ አስተዳደር አመራሮች እየተሳተፉ ነው።
በኦሮሚያ ክልል አስተማማኝ ሰላምና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል
Jul 19, 2026 186
አዳማ፤ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል አስተማማኝ ሰላምና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ እየተካሄደ በሚገኘው የጨፌ ኦሮሚያ መደበኛ ጉባኤ ላይ ባቀረቡት የ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ እንደተናገሩት፥የክልሉ መንግሥት ሰላምን ለማስፈንና የሕግ የበላይነትን ለማስከበር በወሰዳቸው እርምጃዎች ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።   በተለይም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለማድረግ በተሰራው ስራ፣ የክልሉ ህዝብ ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያለውን ጽኑ ፍላጎት በተግባር ያረጋገጠበት መሆኑን ገልጸዋል። ህዝቡ ዝናብና ፀሃይ ሳይበግረው በምርጫው በነቂስ በመሳተፍ፣ ለአፍራሽ አካላት ግልጽ መልዕክት ማስተላለፉንም ፕሬዚዳንቱ አክለዋል። በክልሉ በተለያየ መልክ ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር ሙከራ ቢደረግም፤ በሰላም ወዳዱ ህዝብና በጸጥታ ኃይሎች የተቀናጀ ጥረት መክሸፉን ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል። የክልሉ መንግስት ለዘላቂ ለሰላም መስፈን ባለው ጽኑ ፍላጎት መሰረት የቀረበውን የሰላም አማራጭ በመቀበል ወደ ሰላም የመጡ በሺዎች የሚቆጠሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ መደበኛ ህይወታቸው መመለሳቸውን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። የመንግሥት የሰላም በር አሁንም ክፍት መሆኑን ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ፤ የሰላም አማራጩን ተቀብለው ለሚመጡ ታጣቂዎች በሩ ክፍት ነው ብለዋል። የሰላም አማራጭን ወደ ጎን በመተው በጥፋት ተግባራቸው በሚቀጥሉ አካላት ላይ የክልሉ መንግሥት ጠንካራ የህግ ማስከበር እርምጃ እንደሚወስድ አስገንዝበዋል። በዚህም በክልሉ አስተማማኝ ሰላም ለማስፈንና የህግ የበላይነትን አጠናክሮ ለማስቀጠል መንግሥት በሙሉ አቅሙ እንደሚሰራም ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል።
ጨፌው በክልሉ የሰላም፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ዕቅዶች እንዲሳኩ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል አድርጓል 
Jul 19, 2026 208
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ጨፌው ባለፉት አምስት ዓመታት በክልሉ የሰላም፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ዕቅዶች እንዲሳኩ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ዘርፈ ብዙ ስኬቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን ገለጹ። የጨፌ ኦሮሚያ 6ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ በአዳማ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።   የጨፌው አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ ጨፌው ባለፉት ዓመታት የክልሉን ሕዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎች በታቀደው መሠረት እንዲከናወኑ ድርሻውን ተወጥቷል። በተለይም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ጨፌው የተጣለበትን የሕዝብ አደራ በአግባቡ ሲወጣ መቆየቱን አስታውሰው የሕዝብን ጥቅም የሚያስጠብቁ፣ ሰላም፣ ልማትና ዕድገትን የሚያፋጥኑ በርካታ ውሳኔዎችን ማሳለፉን ተናግረዋል። ሕግ በማውጣት ብቻ የታሰበውን ግብ ማሳካት ስለማይቻል፣ የወጡ ሕጎችና የልማት ዕቅዶች በተግባር ላይ እንዲውሉ ጨፌው ጠንካራ የድጋፍና የክትትል ሥራዎችን ሲያከናውን እንደነበርም አክለዋል። በዚህም በክልሉ በሰላም፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ ልማት መስኮች ተጨባጭ ስኬቶች ሊመዘገቡ መቻላቸውን ጠቁመዋል።   ጉባኤው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸምና ከቀጣይ አቅጣጫዎች እና በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ የሰላምና የልማት ሥራዎች ላይ በጥልቀት በመምከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥም ገልጸዋል። በተጨማሪም የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የጠቅላይ ኦዲት መስሪያ ቤት ሪፖርቶችን መርምሮ ያጸድቃል ተብሎም ይጠበቃል ብለዋል። እንዲሁም የ2019 ዓ.ም የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቅድ ማስፈጸሚያ በጀትን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት መክሮ ያጸድቃል ነው ያሉት።
ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን በትግራይ ወጣቶች ላይ እያደረሰ ያለውን አፈሳ፣ አፈናና ጭቆና ሊያቆም ይገባል
Jul 18, 2026 732
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን በትግራይ ወጣቶች ላይ እያደረሰ ያለው አፈሳ፣ አፈናና ጭቆና ሊያቆም እንደሚገባ በአዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች ገለፁ። ሕገ ወጡ የህወሓት ቡድን በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን አፈና የሚቃወም ሰላማዊ ሰልፍ 'አፈሳ ይቁም፤ ሰላም ይስፈን' በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ተካሂዷል።   ተሳታፊዎቹ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በአሁኑ ወቅት ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን ህገ ወጥ አስገዳጅ አዋጅ በማውጣት፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እና የወጣቶች ሽያጭን ጨምሮ ከፍተኛ ግፍና መከራ እያደረሰ መሆኑን ተናግረዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ምፅላል ገብረሃዋርያ በሰጡት አስተያየት፤ የትግራይ እናቶች ልጆቻቸው እየተገደዱ በመወሰዳቸው በከባድ ሃዘንና ስቃይ ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው ህገ-ወጥ ቡድኑ ይህን ህገወጥ ድርጊት በአስቸኳይ ሊያቆም እንደሚገባ ገልጸዋል። የትግራይ ክልል ወደ ተረጋጋ ሰላምና ልማት እንዲገባ፣ በአዲስ አበባና በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚታዩ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ መሆን እንዳለባትም ተናግረዋል። ለዚህም በተለይ የትግራይ ክልል ወጣቶች ለፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተፈጻሚነትና ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ከፌዴራል መንግስት ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ወይዘሮ ፀሐይ ግርማ በበኩላቸው፤ ህዝቡ ፍፁም ሰላም አግኝቶ እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሰርቶ መለወጥና የልማት ተጠቃሚ መሆን እንደሚፈልግ አመልክተው፤ በዚህም ከመንግስት እየቀረበ ያለውን የሰላም ጥሪ ተቀብሎ የህዝቡን ሰላም ማስቀደም ይገባል ብለዋል። ህገ-ወጡ ህወሓት በትግራይ ክልል ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ እና አፈና በአስቸኳይ ሊቆም እንደሚገባ ገልጸው፤ የትግራይ ህዝብ ምርጫ ሰላምና ልማት ነው ሲሉም ገልጸዋል። አባ ናትናኤል ወልደሰንበት በሰጡት አስተያየት የፕሪቶርያው ስምምነት ከተደረገ በኋላ በትግራይ ክልል ጦርነቱ ቆሞ ሰላም ሰፍኖ ህዝቡ በነፃነት ሲሰራና ሲንቀሳቀስ እንደነበረ አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን ስምምነቱን በማፍረስ የትግራይን ህዝብ ወደ ጦርነትና መከራ ለመክተት እየጣረ እንደሚገኝ ገልፀው፤ ቡድኑ ከድርጊቱ ሊቆጠብ ይገባል ነው ያሉት። በአሁኑ ወቅት በክልሉ እየተካሄደ በሚገኘው አፈሳ ወጣቱ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በመሰደዱ አባቶችና እናቶች ያለረዳት እየቀሩ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡
ፖለቲካ
የትግራይ ሕዝብ ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በትክክል ያንጸባረቀ ስኬታማ ሰልፍ ተካሂዷል 
Jul 19, 2026 76
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የትግራይ ሕዝብ ድምጹን ያሰማበትና ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት በትክክል ያንጸባረቀ ውጤታማ ሰልፍ መካሄዱን የትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት ገለጸ። በትግራይ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን አፈና እና ጭቆና የሚያወግዝ እንዲሁም የጦርነት ዝግጅትን የሚቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ትናንት በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ተካሄዷል። በትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት "አፈሳ ይቁም፣ ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ ሐሳብ በተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በአዲስ አበባና በአካባቢው የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች፣ የሲቪክ ማህበራትና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። ሰልፉን በተመለከተ የትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት መግለጫ ሰጥቷል። የምክር ቤቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አሰፋ ሰልፉን በተመለከተ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ የትግራይ ተወላጆችና ሌሎች የከተማዋ ነዋሪዎች በነቂስ በመውጣት ድምፃቸውን አሰምተዋል። ሰላማዊ ሰልፉ የተለያዩ ዓላማዎችን አንግቦ የተካሄደ ሲሆን፤ ስኬታማ ሆኖ መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ እየፈጸመ ያለው ድርጊት የትግራይን ሕዝብ በእጅጉ እንዳሳሰበው ገልጸው፤ ሰልፉ ስምምነቱ በአስቸኳይ እንዲተገበር የተጠየቀበት መሆኑን ተናግረዋል። ወጣቶች ወደ ጦርነት እንዲገቡ እየተደረገ ያለው አስገዳጅ አፈሳ ወንጀል መሆኑን የገለጹት የምክር ቤቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ፤ ይህንም ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የማሳወቅና ድርጊቱ በአስቸኳይ እንዲቆም መልዕክት የተላለፈበት ሰልፍ እንደነበር አብራርተዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን እያደረገ ያለውን የጦርነት ዝግጅት እንዲያቆም የትግራይ ሕዝብ ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ሰልፍ መሆኑንም ተናግረዋል። ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የሕዝቡን ተቃውሞ ለመመከት መድረኮችን እየጠራ በኃይል ለማስፈራራትና ለማስገደድ መሞከሩን ጠቁመው፤ ሕዝቡ ግን ለሰልፉ ያለውን ድጋፍ ቤቱ በመቀመጥ በተግባር አሳይቷል ብለዋል። ሕዝቡ ትግራይን ድጋሚ ወደ ጦርነት ለመክተት እየተደረገ ያለውን ጥረት አጥብቆ እየተቃወመ እንደሚገኝም አመልክተዋል። የትግራይን ሰቆቃ ለማስቀረት የምንሰራውን ሥራ እናጠናክራለን ያሉት ኃላፊው፤ለዚህም ሁሉም በጋራ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል። ሰልፉ እንዲሳካ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበው፣ መሰል የሕዝብ ድምፅ ማሰሚያ ሰልፎች በሌሎችም አካባቢዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።
ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለመላው ኢትዮጵያዊያን የተላለፈ መልዕክት
Jul 19, 2026 161
በሀገራችን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከናወነ ያለውና ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ የሚመካከሩበት ታሪካዊ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ እንዲሳካ ዜጎች ራሳቸውን ከሀሰተኛ መረጃ በመጠበቅ እና በኮሚሽኑ ላይ ሙሉ እምነት በማሳደር ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥሪ ያቀርባል፡፡ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረውን ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በተመለከተ አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች በማህበራዊ ሚዲያ አውታሮች አማካኝነት ከእውነታ የራቁ መረጃዎችን እያሰራጩ መሆኑን ኮሚሽኑ ደርሶበታል፡፡ ኮሚሽኑ የመናገር ነጻነትን ሙሉ በሙሉ የሚያከብር ገለልተኛ ተቋም እንደመሆኑ ገንቢ የሆኑ ሃሳቦችንና ውይይቶችን የሚቀበል ቢሆንም ሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ በሀሰተኛ መረጃዎች እንዳይታለል አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ ለህዝብ ይፋ ለማድረግ ይገደዳል፡፡ ሀገራዊ ምክክሩ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ነው። የዚህ ሂደት ስኬት የሚወሰነው ዜጎች በትዕግስት፣ በጥበብ እና በጋራ የኃላፊነት ስሜት ለመሳተፍ በሚያሳዩት የጋራ ቁርጠኝነት ላይ ነው። ይህም እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ሂደቱ ተጀመረ እንጂ ውጤቱ ገና ነው፡፡ ይህንን ውጤት በትዕግስት መጠበቅ ደግሞ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚጠበቅ ይሆናል፡፡ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ኮሚሽኑ ባወጣቸው የአሰራር ሂደቶች መሰረት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በዚህ መሰረት ባለፉት አራት ቀናት ኮሚሽኑ የጉባኤው ተሳታፊዎች የተጣለባቸውን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ ማድረግን ጨምሮ ለሂደቱ ጠቃሚ በሆኑ የእውቀት እና የስነ-ልቦና ዝግጅቶች እንዲያደርጉ መደላድሉን ፈጥሯል፤ ይህም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው አንድ አካል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ይህ እየሆነ ባለበት አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ኮሚሽኑ ምክክሩን ለመጀመር እክል እንደገጠመው የተሳሳተ መረጃ ሲያሰራጩ ተመልክተናል፡፡ በመሆኑም መሰል የተሳሳቱ መረጃዎች የራሳቸው ዓላማ ባላቸው ግለሰቦችና ቡድኖች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ስለሚችሉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በየእለቱ የሚኖሩ የምክክር ሂደቶችን ኮሚሽኑ ከሚሰጣቸው መግለጫዎችና የምክክሩን ሂደት ለመዘገብ በስፍራው ከተገኙ መገናኛ ብዙኃን ብቻ በመከታተል ራሱን ከተሳሳቱ መረጃዎች በመጠበቅ የምክክሩን ሂደት እንዲደግፍ ኮሚሽኑ ጥሪ ያቀርባል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም
ጽኑ ሰላምና ልማት እንጂ የሕገ-ወጡን የሕወሓት ቡድን የጦርነት ዳንኪራ አንፈልግም
Jul 19, 2026 122
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የትግራይ ክልል ወጣትና ህዝብ ጽኑ ሰላምና ልማት እንጂ የሕገ-ወጡን የሕወሓት ቡድን የጦርነት ዳንኪራ እንደማይፈልግ የሕገ-ወጡን ቡድን አፈሳና አፈና ሸሽተው አዲስ አበባ የመጡ ወጣቶች ገለጹ። በትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት አስተባባሪነት ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን አፈሳና አፈና በመቃወም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል። ''አፈሳ ይቁም፤ ሰላም ይስፈን'' በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ የክልሉ ተወላጆች፣ ግፍን በመሸሽ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ወጣቶች፣ የሲቪክ ማህበራትና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። አፈሳና አፈናውን በመሸሽ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ወጣቶች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን የክልሉን ወጣቶች በግዳጅ በማፈስ ወደ ጦር ካምፖች እያጋዛቸው ይገኛል። ሕገ-ወጥ ቡድኑም የክልሉን ወጣቶች ለሱዳንና ሻቢያ የጥፋት ኃይሎች በመሸጥ ሰብዓዊ ክብርን የሚጋፋ ኢ-ሰብዓዊ ግፍ እየፈጸመ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወጣት ሶሎሞን እምባዬ፤ ጦርነት ናፋቂው ሕገ-ወጥ ቡድን ካለፈው ስህተቱ ሳይማር ለዳግም ጦርነት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ ገልጿል። የጦርነት ነጋዴው ሕገ-ወጥ ቡድን ፅምዶ በተሰኘ የጥፋት ጥምረት ወጣቶችን በየቤተ-ዕምነቱ፣ በገበያና በየመንገዱ ለቅሞ በመውሰድና ለውጭ ገበያ ጭምር በመሸጥ እናቶችን እያስለቀሰ መሆኑን ተናግሯል። የትግራይ ሕዝብ ፍላጎት ጽኑ ሰላምና ልማት ብቻ መሆኑን ያነሳው ወጣቱ፤ እናቶችም የጦር መሳሪያ ካነገበው ኃይል ጋር በመጋፈጥ ተቃውሟቸውን እያሰሙ መሆናቸውን አክሏል። ፌዴራል መንግሥትም የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በማፍረስ ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን ከፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በፈጠረው የጥፋት ጥምረት በሕዝቡ ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና መከራ እንዲያስቆም ጥሪ አቅርቧል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወጣት እምሩ ብርሃኑ በበኩሉ፤ ሕገ-ወጡ ቡድን ወጣቶችን ለውጭ ኃይሎች በመሸጥ የገቢ ምንጭ ማድረጉ የአደባባይ ምስጢር ከሆነ መሰነባበቱን ገልጿል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ወጣቶችና ሕዝብም የቡድኑን የጦርነት ጉሰማ በመታገል ሰላም ፈላጊነታቸውን በተግባር ሊያሳዩ እንደሚገባ አሳስቧል። ወጣት መብራህቱ ኻልአዩ በበኩሉ፤ ቡድኑ በክልሉ የከፈተው የአፈሳና የአፈና ጭቆና ሕዝብን ለስቃይ፣ ወጣቶችን ደግሞ ለስደት መዳረጉን ጠቁሟል። አክሎም ቡድኑ ወጣቶችን በማፈን ከሚፈፅመው ግፍ በተጨማሪም አርሶ አደሩ የእርሻ ሥራውን በአግባቡ እንዳያከናውን ተጽዕኖ እየፈጠረ መሆኑን ተናግሯል።
በክልሉ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማስተባበር በተሰራው ሥራ ውጤት ተገኝቷል
Jul 19, 2026 179
ቦንጋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በክልሉ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማስተባበር በተሰራው ሥራ ውጤት መገኘቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። የክልሉ የፓርቲና መንግስት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡   መድረኩን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ የአመራሩን የመፈጸም አቅም በማቀናጀት በበጀት ዓመቱ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ፣ በመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥም ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማስተባበር በተሰራው ሥራ ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል። የግብርናውን ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ባለፈ የኩታ ገጠም አሰራርን በመተግበር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ጥረት መደረጉንም አንስተዋል፡፡ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የሻይና ቡና ልማትን ለማሳካት በርብርብ መሰራቱን አስታወሰው፤ በበጀት ዓመቱ 61 ሺህ ቶን የታጠበና ያልታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡንም ኢንጂነር ነጋሽ (ዶ/ር) ገልፀዋል።   የማዕድል ልማትን በተገቢው በመምራትም 348 ኪ.ግ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደተቻለ ጠቅሰው፣ የክልሉን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ በተደረገ ሰፊ ርብርብም ከ18 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ተናግረዋል። በመድረኩ በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት እና የክልሉ መንግስት የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2019 በጀት የዓመት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል። በመድረኩ የክልሉ፣ የዞኖች እና የከተማ አስተዳደር አመራሮች እየተሳተፉ ነው።
በኦሮሚያ ክልል አስተማማኝ ሰላምና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል
Jul 19, 2026 186
አዳማ፤ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል አስተማማኝ ሰላምና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ እየተካሄደ በሚገኘው የጨፌ ኦሮሚያ መደበኛ ጉባኤ ላይ ባቀረቡት የ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ እንደተናገሩት፥የክልሉ መንግሥት ሰላምን ለማስፈንና የሕግ የበላይነትን ለማስከበር በወሰዳቸው እርምጃዎች ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።   በተለይም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለማድረግ በተሰራው ስራ፣ የክልሉ ህዝብ ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያለውን ጽኑ ፍላጎት በተግባር ያረጋገጠበት መሆኑን ገልጸዋል። ህዝቡ ዝናብና ፀሃይ ሳይበግረው በምርጫው በነቂስ በመሳተፍ፣ ለአፍራሽ አካላት ግልጽ መልዕክት ማስተላለፉንም ፕሬዚዳንቱ አክለዋል። በክልሉ በተለያየ መልክ ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር ሙከራ ቢደረግም፤ በሰላም ወዳዱ ህዝብና በጸጥታ ኃይሎች የተቀናጀ ጥረት መክሸፉን ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል። የክልሉ መንግስት ለዘላቂ ለሰላም መስፈን ባለው ጽኑ ፍላጎት መሰረት የቀረበውን የሰላም አማራጭ በመቀበል ወደ ሰላም የመጡ በሺዎች የሚቆጠሩ የቀድሞ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ መደበኛ ህይወታቸው መመለሳቸውን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። የመንግሥት የሰላም በር አሁንም ክፍት መሆኑን ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ፤ የሰላም አማራጩን ተቀብለው ለሚመጡ ታጣቂዎች በሩ ክፍት ነው ብለዋል። የሰላም አማራጭን ወደ ጎን በመተው በጥፋት ተግባራቸው በሚቀጥሉ አካላት ላይ የክልሉ መንግሥት ጠንካራ የህግ ማስከበር እርምጃ እንደሚወስድ አስገንዝበዋል። በዚህም በክልሉ አስተማማኝ ሰላም ለማስፈንና የህግ የበላይነትን አጠናክሮ ለማስቀጠል መንግሥት በሙሉ አቅሙ እንደሚሰራም ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል።
ጨፌው በክልሉ የሰላም፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ዕቅዶች እንዲሳኩ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል አድርጓል 
Jul 19, 2026 208
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ጨፌው ባለፉት አምስት ዓመታት በክልሉ የሰላም፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ዕቅዶች እንዲሳኩ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ዘርፈ ብዙ ስኬቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን ገለጹ። የጨፌ ኦሮሚያ 6ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ በአዳማ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።   የጨፌው አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሰዓዳ አብዱራህማን በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ ጨፌው ባለፉት ዓመታት የክልሉን ሕዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎች በታቀደው መሠረት እንዲከናወኑ ድርሻውን ተወጥቷል። በተለይም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ጨፌው የተጣለበትን የሕዝብ አደራ በአግባቡ ሲወጣ መቆየቱን አስታውሰው የሕዝብን ጥቅም የሚያስጠብቁ፣ ሰላም፣ ልማትና ዕድገትን የሚያፋጥኑ በርካታ ውሳኔዎችን ማሳለፉን ተናግረዋል። ሕግ በማውጣት ብቻ የታሰበውን ግብ ማሳካት ስለማይቻል፣ የወጡ ሕጎችና የልማት ዕቅዶች በተግባር ላይ እንዲውሉ ጨፌው ጠንካራ የድጋፍና የክትትል ሥራዎችን ሲያከናውን እንደነበርም አክለዋል። በዚህም በክልሉ በሰላም፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ ልማት መስኮች ተጨባጭ ስኬቶች ሊመዘገቡ መቻላቸውን ጠቁመዋል።   ጉባኤው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸምና ከቀጣይ አቅጣጫዎች እና በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ የሰላምና የልማት ሥራዎች ላይ በጥልቀት በመምከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥም ገልጸዋል። በተጨማሪም የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የጠቅላይ ኦዲት መስሪያ ቤት ሪፖርቶችን መርምሮ ያጸድቃል ተብሎም ይጠበቃል ብለዋል። እንዲሁም የ2019 ዓ.ም የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቅድ ማስፈጸሚያ በጀትን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት መክሮ ያጸድቃል ነው ያሉት።
ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን በትግራይ ወጣቶች ላይ እያደረሰ ያለውን አፈሳ፣ አፈናና ጭቆና ሊያቆም ይገባል
Jul 18, 2026 732
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን በትግራይ ወጣቶች ላይ እያደረሰ ያለው አፈሳ፣ አፈናና ጭቆና ሊያቆም እንደሚገባ በአዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች ገለፁ። ሕገ ወጡ የህወሓት ቡድን በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን አፈና የሚቃወም ሰላማዊ ሰልፍ 'አፈሳ ይቁም፤ ሰላም ይስፈን' በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ተካሂዷል።   ተሳታፊዎቹ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በአሁኑ ወቅት ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን ህገ ወጥ አስገዳጅ አዋጅ በማውጣት፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እና የወጣቶች ሽያጭን ጨምሮ ከፍተኛ ግፍና መከራ እያደረሰ መሆኑን ተናግረዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ምፅላል ገብረሃዋርያ በሰጡት አስተያየት፤ የትግራይ እናቶች ልጆቻቸው እየተገደዱ በመወሰዳቸው በከባድ ሃዘንና ስቃይ ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው ህገ-ወጥ ቡድኑ ይህን ህገወጥ ድርጊት በአስቸኳይ ሊያቆም እንደሚገባ ገልጸዋል። የትግራይ ክልል ወደ ተረጋጋ ሰላምና ልማት እንዲገባ፣ በአዲስ አበባና በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚታዩ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ መሆን እንዳለባትም ተናግረዋል። ለዚህም በተለይ የትግራይ ክልል ወጣቶች ለፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተፈጻሚነትና ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ከፌዴራል መንግስት ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ወይዘሮ ፀሐይ ግርማ በበኩላቸው፤ ህዝቡ ፍፁም ሰላም አግኝቶ እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሰርቶ መለወጥና የልማት ተጠቃሚ መሆን እንደሚፈልግ አመልክተው፤ በዚህም ከመንግስት እየቀረበ ያለውን የሰላም ጥሪ ተቀብሎ የህዝቡን ሰላም ማስቀደም ይገባል ብለዋል። ህገ-ወጡ ህወሓት በትግራይ ክልል ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ እና አፈና በአስቸኳይ ሊቆም እንደሚገባ ገልጸው፤ የትግራይ ህዝብ ምርጫ ሰላምና ልማት ነው ሲሉም ገልጸዋል። አባ ናትናኤል ወልደሰንበት በሰጡት አስተያየት የፕሪቶርያው ስምምነት ከተደረገ በኋላ በትግራይ ክልል ጦርነቱ ቆሞ ሰላም ሰፍኖ ህዝቡ በነፃነት ሲሰራና ሲንቀሳቀስ እንደነበረ አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ ህገ-ወጡ የህወሓት ቡድን ስምምነቱን በማፍረስ የትግራይን ህዝብ ወደ ጦርነትና መከራ ለመክተት እየጣረ እንደሚገኝ ገልፀው፤ ቡድኑ ከድርጊቱ ሊቆጠብ ይገባል ነው ያሉት። በአሁኑ ወቅት በክልሉ እየተካሄደ በሚገኘው አፈሳ ወጣቱ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በመሰደዱ አባቶችና እናቶች ያለረዳት እየቀሩ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡
ማህበራዊ
የአዲስ አበባ ልማት ውጤቶች ለሰው ልጆች መኖሪያነት የሚገባን ክብር በተግባር የገለጡ ናቸው
Jul 19, 2026 31
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ውጤቶች ለሰው ልጆች መኖሪያነት የሚገባን ክብር በተግባር የገለጡ መሆናቸውን የክፍለ ከተማ ሥራ አስፈጻሚዎች ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሄድ የቆየውን የ2018 በጀት ዓመትና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በስኬት አጠናቋል። በበጀት ዓመቱም ከተማ አስተዳደሩ በጥቅሉ ከ96 በመቶ በላይ የአፈጻጸም ውጤት ማስመዝገብ እንደቻለ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በግምገማ መድረኩ፤ በበጀት ዓመቱ ለመፈጸም የተቀመጡ ግቦች አመርቂ ውጤት እንደተገኘባቸው አስረድተዋል። በግምገማው የተሳተፉት የአራዳና የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የመዲናዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በማሳደግ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስኬቶች ተመዝግበዋል። የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማቱም የመዲናዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ በመገንባት፣ ለነዋሪዎቿ ተገቢውን ክብር የምትሰጥ ከተማ እንድትሆን ማድረጉን ገልጸዋል።   የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወንድሙ ዑመር ፤ አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ክብር የሚሰጥ የከተማ ገጽታ በመላበስ፣ አስደማሚ የልማት ስኬቶች የሚመዘገቡባት ከተማ እየሆነች ነው ብለዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥና አዲስ የከተሜነት መኖሪያ ደረጃ ያሸጋገረ የልማት ባህል መፈጠሩን ገልጸዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኮሪደር፣ በወንዝ ዳርቻና በሰው-ተኮር የልማት መርሃ ግብሮች የተገኙ አመርቂ ውጤቶችም ነዋሪዎችን ከውስብስብ ችግሮች በማላቀቅ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።   የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታረቀኝ ወርቅነህ በበኩላቸው፤ አዲስ አበባ ውብና ማራኪ ገጽታን የተጎናጸፈች የአለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ማዕከል መሆኗን ገልጸዋል። በመዲናዋ የተገነቡ ጽዱ፣ ውብና ምቹ የልማት ስኬቶች፣ በተለይም የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርና ሌሎች ሰው-ተኮር ፕሮጀክቶች የዜጎችን ሕይወት በመቀየር ረገድ አመርቂ ውጤት ማስመዝገባቸውን አስረድተዋል።
ሁሉም ተቋማት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን የበለጠ በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ማስቀጠል ይጠበቅባቸዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 19, 2026 44
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሁሉም ተቋማት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶችን የበለጠ በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች "ትጋት ያሸልማል" በሚል መሪ ቃል የዕውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጀት ዓመቱ የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎችን በመሥራት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቢሮዎች፣ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ዕውቅናና ሽልማት አበርክተዋል። በዚሁ መሰረት የካቢኔ አባል ከሆኑና ከተሽከርካሪ ተሸላሚ ከሆኑ ቢሮዎች መካከል ሰላምና ጸጥታ፣ ጤና፣ ገቢዎች፣ ዲዛይንና ግንባታ እንዲሁም የትምህርት ቢሮዎች ይገኙበታል። የለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከልም ልዩ ሽልማት የተበረከተለት ሲሆን፤ በከተማ አስተዳደሩ የቦሌ፣ ለሚኩራና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች በተመሳሳይ የተሽከርካሪ ተሸላሚ ሆነዋል። የካቢኔ አባል ያልሆኑት የደንብ ማስከበር ባለስልጣን፣ የመንገዶች ባለስልጣን፣ የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን፣ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለስልጣን፣ እንዲሁም የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ተሸከርካሪ ተሸልመዋል። በተጨማሪም በሁሉም ክፍለ ከተማ ውስጥ ካሉ ወረዳዎች ከአንድ እስከ ሶስት የወጡ 33 ወረዳዎች ተሸላሚ ሲሆኑ፤ የፋይናንስ፣ የኢንዱስትሪ ልማት፣ የኮሙኒኬሽን፣ የንግድና ፍትሕ ቢሮዎችም የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።   ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት ፤ በ2018 በጀት ዓመት በተያዙ ዕቅዶች መሰረት ከ96 በመቶ በላይ የአፈጻጸም ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ መዋቅሮች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና በሌሎች መስኮች ላስመዘገቡት ውጤታማ የልማት አፈጻጸሞች ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም ሁሉም ተቋማት የተገኙ ስኬቶችን የበለጠ በማሳደግና ክፍተቶችን በመሙላት ለተሻለ የልማት ስኬት ገንቢ ሚና መጫወት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው፤ ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ ታላላቅ ኮንፈረንሶች፣ ህዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት በስኬት እንዲከበሩ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።   ተቋማቸው የተሸለመው በኤሌክትሪክ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለቀጣይ ሥራ ትልቅ ኃላፊነት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ በበኩላቸው፤ የተበረከተላቸው የኤሌክትሪክ መኪና ሽልማት በጤናው ዘርፍ ለተመዘገበው ስኬታማ አፈጻጸም የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን ገልጸዋል።   በከተማው 68 የጤና ተቋማት የመረጃ አያያዝን ወረቀት-አልባ በማድረጋቸው እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በተከናወኑ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን አስረድተዋል። የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አደፍርስ ኮራ በበኩላቸው፤ በክፍለ ከተማዋ የመዲናዋን ውብ ገጽታ የሚያላብሱ ስኬታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።   ክፍለ ከተማው የተሰጠው ሽልማትም የልማት አጋሮችን በማስተባበር በኮሪደር፣ በመንገድ፣ በወጣቶች መዝናኛና ስፖርት ማዘውተሪያ ላይ ላስመዘገበው የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን ተናግረዋል።
ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን የመደጋገፍ ባህል እያጎለበተ ነው
Jul 19, 2026 44
ጅግጅጋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን የእርስ በርስ መደጋገፍና ግንኙነት እያጎለበተ መምጣቱን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ገለጸ። "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የዘንድሮ ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊዎች በሶማሌ ክልል የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራትን አከናውነዋል። ወጣቶቹ በጅግጅጋ ከተማ ደም ከመለገስ ባለፈ የአቅመ ደካማ ወገኖችን መኖሪያ ቤቶች የመገንባት መርሐግብር አከናውነዋል። በመርሀግብሩ ላይ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የበጎፈቃድ ከፍተኛ ባለሙያ እና የቡድኑ አስተባባሪ እንደገና ፍቃዱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በእርስ ግንኙነት የሚጠናከርበትና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች የሚከናወኑበት ነው።   ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች ሀገር መሆኗን አስታውሰው፣ ወጣቶቹ ለአንድ ዓላማ መሰባሰባቸው ግንኙነታቸውን ከማጠናከር ባለፈ በሚደርሱባቸው አካባቢዎች የባህል ልውውጥ ለማድረግ ያስችላቸዋል ብለዋል። የሚሰጡት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትም የህብረተሰቡን ማህበራዊ ችግር በማቃለል አብሮነትን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ነው የገለጹት። በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከሀገሪቱ ሁሉም ክልሎች የተውጣጡ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች በማከናወን ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል። በዚህም በተለይ በአካባቢ ጥበቃ፣ አቅመ ደካማ ወገኖችን በተለያየ መንገድ በመደገፍ እንዲሁም በትምህርት፣ በጤና እና በተለያዩ የልማት ዘርፎች በመሰማራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመዲናዋ የመኖሪያ ቤት ፍላጎትና አቅርቦትን የሚያቀራርብ አማራጭ የቤት ልማት መርሃ ግብር እየተከናወነ ነው
Jul 19, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የመኖሪያ ቤት ፍላጎትና አቅርቦቱን የሚያቀራርብ ስኬታማ የብዝኅ ቤት ልማት አማራጭ መርሃ ግብር እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሄድ የቆየውን የ2018 በጀት ዓመት እና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በስኬት አጠናቋል። በበጀት ዓመቱም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጥቅሉ ከ96 በመቶ በላይ የአፈጻጸም ውጤት ማስመዝገብ እንደቻለ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በግምገማ መድረኩ ፤ በበጀት ዓመቱ ለመፈጸም የተቀመጡ ግቦች አመርቂ ውጤት እንደተገኘባቸው አስረድተዋል። በግምገማው የተሳተፉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በቤት ልማት ዘርፍ ውጤታማ ሥራዎች ተሰርተዋል። ለአብነትም በመንግሥት፣ በግልና መንግሥት አጋርነት እንዲሁም በግል ባለሃብቶች ብዝኅ የቤት ልማት አማራጭ መርሃ ግብር የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ፍላጎትና አቅርቦት የሚያቀራርብ ስኬታማ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህ ጥረትም ከዚህ ቀደም የነበረውን የቤት አቅርቦት እጥረት በመቅረፍ በመደመር እይታ አመርቂ የቤት ልማት ውጤት ማምጣት እየተቻለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በ2018 በጀት ዓመት በመንግሥት በጀት ብቻ ግንባታቸው የተጠናቀቁና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ 50 ሺህ 305 ቤቶች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዳሴው ግድብ ምርቃት ወቅት ባበሰሩት የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶች ግንባታ መርሃ ግብር፤ የመኖሪያ ቤት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ማስገንዘባቸው ይታወሳል።
ኢኮኖሚ
ጨፌ ኦሮሚያ ለክልሉ መንግሥት የ2019 በጀት ዓመት ሥራ ማስፈጸሚያ 704 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ
Jul 19, 2026 37
አዳማ፣ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ጨፌ ኦሮሚያ ለተያዘው በጀት ዓመት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል 704 ቢሊዮን ብር በጀት በሙሉ ድምፅ አጸደቀ። ጨፌ ኦሮሚያ በ6ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤው የዛሬ ውሎ የክልሉን መንግሥት የ2019 በጀት አጽድቋል። የኦሮሚያ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶሎሳ ገደፋ የበጀት ዝርዝሩን ለጨፌው ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በጀቱ ከተረጂነት ለመውጣትና ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብና ስትራቴጂ ለማሳካት ያለመ ነው። የበጀት ድልድሉም የልማት ፕሮግራሞችን መሠረት በማድረግና የክልሉን ዕድገት ለማፋጠን በሚያስችል መልኩ ተከናውኗል ብለዋል። የልማት ዕቅዱን ውጤታማ ለማድረግ ከሁሉም የክልሉ ሴክተር ተቋማት ጋር ውይይት መደረጉን የጠቀሱት ኃላፊው፤ ትኩረት ለሚሹ ጉዳዮች በበጀት ድልድሉ ቅድሚያ መሰጠቱን ተናግረዋል።   በጀቱ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ76 በመቶ ጭማሪ ያለው ሲሆን፣ የበጀት ድልድሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ በተለይም በከተሞችና በወረዳዎች ለሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል ብለዋል። በዚህም መሠረት ለጤና፣ ለትምህርት እና ለመንገድ መሠረተ ልማት አንዲሁም ለመስኖ እና ለንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ቅድሚያ ተሰጥቷል ነው ያሉት። ይህ በጀት በከተሞችና በወረዳዎች መካከል ሊኖር የሚችለውን የመሠረተ ልማት ልዩነት ለማጥበብና በክልሉ ቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ሰፋፊ መሬቶችን ለማልማት የሚያስችሉ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ታሳቢ ማድረጉንም ኃላፊው ገልጸዋል። ከተሞችና ወረዳዎች የሚሰጣቸውን በጀት ለማኅበራዊ መሠረተ ልማት ማዋል ላይ ትኩረት አድርገው መደልደል እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ማንኛውንም የገቢ ዓይነት ያለ ሕጋዊ ደረሰኝ መሰብሰብ የተከለከለና የሕግ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑንም አሳስበዋል። የጨፌው አባላት በቀረበው የበጀት ቀመር ላይ በሰጡት አስተያየት፤ የበጀት ድልድሉ ከተረጂነት ለመውጣትና ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ከበጀት ድልድሉ ባለፈ፣ የካፒታል በጀትን ጨምሮ የተመደበው ሀብት ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ በዋና ዋና የልማት ዘርፎች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተመዝግበዋል
Jul 19, 2026 91
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ በዋና ዋና የልማት ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸው ተገለጸ። እየተካሄደ ባለው የጨፌ ኦሮሚያ 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የጨፌው አባላት የሰላም ማስፈንና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ሥራዎችን የተመለከቱ ጥያቄዎችን አንስተዋል። ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የክልሉ መንግስት የተለያዩ ዘርፎች የሥራ መሪዎች በበጀት ዓመቱ ተስፋ ሰጪ ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል። የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደርና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ፤ የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ በተከናወነው የተቀናጀ ሥራ የክልሉ ሰላም እየተሻሻለ መጥቷል ብለዋል።   ህብረተሰቡ እና መንግስት በጋራ በሰሩት ሥራ የክልሉ ሰላም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሰው፣ ለዚህም በክልሉ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። መንግስት የክልሉን የጸጥታ አካላት አቅም ለማጠናከር ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ሲሆን፣ ይህንን ለማሳካትም አቅም የመገንባትና የማብቃት ሥራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን አመልክተዋል። አሁንም በክልሉ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት የቀረበላቸውን የሰላም ጥሪ የሚቀበሉ ከሆነ የክልሉ መንግስት ለመነጋገር ዝግጁ ሆኖ እየጠበቀ ይገኛል ሲሉም ገልጸዋል። በሌላ በኩል የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት የጀመረው ሥራ ስኬታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቶላ ባሪሶ ገልጸዋል።   በክልሉ የትምህርት ሥራ በጥሩ ሂደት ላይ መሆኑን ያነሱት ኃላፊው፣ ተማሪዎች በሥነ-ምግባር ታንጸውና ብቁ ዜጋ ሆነው እንዲወጡ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል ብለዋል። በተመሳሳይ በክልሉ የአርብቶ አደሩን ሕይወት ለመለወጥ በተከናወነው ሥራ አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን የክልሉ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ ተናግረዋል።   ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ሥራዎች 512 የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉን ገልጸዋል። የክልሉ መንገዶችና ሎጂስቲክስ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ሄለን ታምሩ በበኩላቸው የሕዝቡ የመንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እየተመለሱ መሆኑን ተናግረዋል።   በተለይም የኮንትራክተሮች አቅም ማነስ፣ የኮንስትራክሽን ዕቃዎች ዋጋ ንረትና በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ የሚታየው የጸጥታ ችግር ለመንገድ ፕሮጀክቶች መጓተት ምክንያት እንደሆኑ ጠቅሰው፣ እነዚህን ችግሮች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመፍታት የመንገድ ስራዎችን ለማፈጠን ይሰራል ብለዋል። የክልሉን የመጠጥ ውሃ ተደራሽነት ለማሳደግ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ በተሰራው ስራ የክልሉን የንጹህ መጠጥ ውኃ ሽፋን ማሳደግ መቻሉን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ሚሊዮን በቀለ ናቸው።   ቢሮው ከመንግስት በጀት በተጨማሪ የማኅበረሰቡን እና የአጋር አካላትን ተሳትፎ በመጠቀም የመጠጥ ውሃ ሽፋንን ለማሳደግ ተጨባጭ ሥራ ሰርቷል ብለዋል።
የአዲስ አበባ ሁለንተናዊ የልማት ስኬቶች ስምን ከግብር በማሰናሰል የተገኙ ውጤቶች ናቸው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 19, 2026 105
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ሁለንተናዊ የልማት ስኬቶች ስምን ከግብር በማሰናሰል የተገኙ ውጤቶች መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የ2018 በጀት ዓመት እና የአምስት ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በስኬት አጠናቋል።   የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የከተማ አስተዳደሩ በ2018 በጀት ዓመት ከ96 በመቶ በላይ የአፈጻጸም ውጤት አስመዝግቧል። በመዲናዋ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች ከተማዋን ውብና ጽዱ ከማድረጋቸውም በላይ ዓለም አቀፍ እውቅና ጭምር እንዳስገኙ ገልጸዋል። የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት፣ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በማሳካት፣ እንዲሁም ግልጽነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መቻሉንም አስታውቀዋል። የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር ዓባይ በበኩላቸው፤ ባለፉት አምስት ዓመታት መዲናዋን ማራኪ ገጽታ በማላበስ ረገድ ሁለንተናዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። የተገኙት ውጤቶችም የሕዝብን ጥያቄዎች ምላሽ በማስገኘት እና ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት በመፈጸም ረገድ የታየው የአመራር ቁርጠኝነት ውጤት መሆናቸውን አስረድተዋል። በቀጣይም የተገኙ ስኬቶችን በማስቀጠልና ክፍተቶችን በማረም የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎች እንደሚከናወኑ አረጋግጠዋል። በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ በበኩላቸው፤ በ2018 በጀት ዓመት የከተማዋን እና የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያፋጥኑ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም የመዲናዋን በጎ ገጽታ በማጎልበት እና የሕዝቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ተጨባጭ ውጤቶችን ማምጣት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ሚሊዮን ማቴዎስ፤ በመዲናዋ የሚከናወኑ ቁልፍ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል እየፈጠሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የኢንዱስትሪ፣ የከተማ ግብርና፣ የኮንስትራክሽንና የአገልግሎት ዘርፎች የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ያላቸው ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነም አክለዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀምበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዲጂታል መንግሥት አገልግሎት የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በአንድ ማዕከል አገልግሎት የተጀመረውን የዘመናዊ አሠራር አቅም ይበልጥ በማጠናከር ተደራሽነቱን እንደሚያሰፉ አስረድተዋል።  
የግብር አሰባሰብ አቅምን በማሳደግ የከተሞችን የመሰረተ ልማት ተደራሽነት በራስ አቅም ለማሳካት ትኩረት ተሰጥቷል
Jul 19, 2026 95
ቡታጅራ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተሞችን የግብር አሰባሰብ አቅም በማሳደግ የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን በራስ አቅም ለማሳካት በቅንጅት እንደሚሰራ ተገለጸ። በክልሉ የከተሞቹን እንቅስቃሴ በማሳለጥና ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን በማሳደግ ገቢያቸውን ከማሳደግ ባለፈ የማህበረሰቡን የልማት ጥያቄ በራሳቸው መፍታት እንዲችሉ ለቅንጅታዊ ሥራ ትኩረት ተሰጥቷል። በተያዘው የ2019 በጀት ዓመትም ይህን ተግባር ለማስቀጠል አሳታፊ እቅዶችን በማውጣት ወደስራ መገባቱ ተመላክቷል። ኢዜአ ያነጋገራችው የሆሳዕና፣ ቡታጅራ እና ወልቂጤ ከተሞች ገቢ ጽህፈት ቤቶች የሥራ ሃላፊዎች እንዳሉት በተያዘው የ2019 በጀት ዓመት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ልማትን ለማፋጠን አቅደው ወደ ተግባር ገብተዋል። በዚህም ለማህበረሰቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ለመስጠት ለቅንጅታዊ አሰራርና ግብር ስወራን ለመቆጣጠር ትኩረት መስጠታቸውን ተናግረዋል። የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አውላቸው ዮሐንስ እንደገለጹት ፤ በከተማው በበጀት ዓመቱ 4 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል። ገቢውን ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸው በእዚህም ለማህበረሰቡ የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በቅንጅት ይሰራል ብለዋል። ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች እና በደረሰኝ የሚሰበሰበው ገቢ ላይ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን በማረም ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ ለአካባቢው ፈጣን እድገት በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል። የቡታጅራ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ወልዩ ከበደ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ከተማው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የልማት ሥራዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን ግብ ተይዞ ወደ ተግባር ተገብቷል። በተያዘው የ2019 በጀት ዓመት በከተማው ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱንም አመልክተው፣ በተለይም በአገልግሎት ዘርፍ የሚገኝን ገቢ በማሳደግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል ብለዋል። ገቢን በማሳደግ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎችን ለማከናወን ግንዛቤ ከመፍጠር ጀምሮ የታክስ ህግ የማስከበር ሥራ በቅንጅት እንደሚሰራ የተናገሩት ደግሞ የወልቂጤ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ይድረሱ ተስፋዬ ናቸው። እንደሃላፊው ገለጻ በበጀት ዓመቱ በከተማው 1 ቢሊዮን 77 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል። የግብር አሰባሰብ ሥርአቱን ከማዘመን ባለፈ የግብር ከፋዩን ለግዢ ደረሰኝ የመስጠት ባህልን ለማሳደግና ለህግ ተገዢ እንዲሆን የማድረግ ሥራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑንም አመልክተዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሕዝብና መንግሥትን መተማመን እያጎለበተ ነው 
Jul 19, 2026 79
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለው መተማመን እንዲጎለብት ማድረጉን የአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ደሳለኝ ተረፈ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የ2018 በጀት ዓመት እና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈፃጸም ግምገማ በስኬት አጠናቋል። በዚሁ መድረክ ላይ ከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ በጥቅሉ ከ96 በመቶ በላይ የሚሆን የአፈፃጸም ስኬት ማስመዝገብ እንደቻለ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ መድረኩ በበጀት ዓመቱ ለመፈጸም የተቀመጡ ታላላቅ ግቦች እንዲሁም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ስትራቴጂክ ዕቅዶች ምን ያህል ውጤታማ በሆነ መንገድ እንደተከናወኑ በጥልቀት የተገመገመበት መሆኑን ገልጸዋል። የአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ደሳለኝ ተረፈ፤ ቀደም ሲል ከፍተኛ ስብራት የነበረበትን የአገልግሎት ዘርፍ ለማሻሻል እና የህዝቡን እርካታ ለማረጋገጥ ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከተማ አስተዳደሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ የተጀመረው ዘመናዊው የአዲስ መሶብ ዲጂታል አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ 11 ቋሚ ቦታዎች እና አንድ ተንቀሳቃሽ ማዕከል ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የ 25 ተቋማትን 150 የተለያዩ አገልግሎቶች በአንድ ጣራ ስር በማስተናገድ ላይ የሚገኘው ይህ ስኬታማ የዲጂታል ሽግግር ፕሮጀክት፣ በቀጣይም ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋፋት በልዩ ትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ አብራርተዋል። የአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመር የህብረተሰቡን የዘመናት ምሬት በዘላቂነት የፈታ ሲሆን፣ በአገልግሎቱም የህዝቡን እርካታ በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ተችሏል። ይህ ዘመናዊ አሰራር ህዝቡ የሚፈልገውን አገልግሎት በአንድ ማዕከል በቀላሉ እንዲያገኝ በማድረግ በመንግስትና በህብረተሰቡ መካከል ያለውን የጋራ መተማመን ይበልጥ ማጎልበት መቻሉን ገልጸዋል።
በአማራጭ ኢነርጂ ማህበረሰቡን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Jul 19, 2026 153
አሶሳ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአማራጭ ኢነርጂ ተደራሽነትን በማስፋፋት ማህበረሰቡን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራት እንደሚጠናከሩ አስታወቀ። ሚኒስቴሩ የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም አተገባበር ላይ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የዘርፉ አመራሮች እና ባለሙያዎች ጋር በአሶሳ ከተማ መክሯል።   በመድረኩ ላይ የተገኙት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ አስተማማኝ፣ ተመጣጣኝና ቀጣይነት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት የመሰረተ ልማት ግብ ብቻ ሳይሆን የዜጎችን ሕይወት ያቃልላል። የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝ እና ተደራሽ ለማድረግ የኢነርጂ ፖሊሲ ወጥቶ ሥራ ላይ መዋሉን ገልፀው፣ ፖሊሲው የግሉን ዘርፍ የሚያበረታታ እና የኃይል ተደራሽነትን የሚያሳድግ መሆኑን አስረድተዋል። ብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም በተለይም በገጠራማ አካባቢዎች የሶላር ኢነርጂ ተጠቃሚነትን የሚያሳድግ እና በደን ጭፍጨፋ በአካባቢ ላይ የሚደርስን ተፅዕኖ የሚቀንስ ነው ብለዋል። አማራጭ የታዳሽ ኃይል ተደራሽነትን በማስፋፋት ህብረተሰቡን የሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ የኃይል መሠረተ ልማት ዝርጋታ እና አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል።   የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ታሪኩ ኩመራ በበኩለቸው፤ በፕሮግራሙ በክልሉ የተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎች በገጠሩ አካባቢ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋሉ መምጣታቸውን እና ይህም በርካታ ዜጎችን ከድካም መታደጉን ተናግረዋል። የተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችን የሚያመርቱ ማህበራትን መደገፍ ዜጎች ማገዶ ፍለጋ የሚያባክኑትን ጊዜና ጉልበት ለመቀነስና የአየር ብክለትን ለመከላከል ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ጠቅሰዋል። ለሁለት ቀን በሚቆየው መድረክ በክልሉ በአነርጂ ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት ላይ ምክክር እንደሚደረግ ተመላክቷል።
ኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ቀድሞ በመከላከል አቅም ገንብቶ በማየታችን ኮርተናል
Jul 18, 2026 675
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን መከላከልና ለወረርሽኞች የተቀናጀና ሳይንሳዊ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም በመገንባቱ ኩራት እንደተሰማቸው ተቋሙን ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ ሠራተኞችና የቀድሞ አመራር ገለጹ። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ኹነቶች ያከበረ ሲሆን፣ ተቋሙን ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅና ተሰጥቷቸዋል።   እውቅና ከተሰጣቸው መካከል ተቋሙን ለ25 ዓመታት ከተመራማሪነት እስከ ዋና ዳይሬክተርነት ያገለገሉት ዶክተር አምሃ ከበደ አንዱ ናቸው። የቀድሞው ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አምሃ በተለያየ የሙያና የኃላፊነት እርከን በማገልገል የተቋሙ የምዕተ ዓመት ታሪክ ላይ አስተዋፅኦ ማበርከታቸው እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ዓመታት ባካሄዳቸው መዋቅራዊ ሪፎርሞች ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ቀድሞ የመከላከል አቅሙን በማሳደጉ ኩራት እንደተሰማቸው ገልፀዋል። ኮቪድ-19ን ጨምሮ በቅርቡ የተከሰቱትን ኤምፖክስና ማርበርግ የመሰሉ ወረርሽኞችን በተቀናጀ፣ ፈጣንና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በመመከት በኩል ያስመዘገበው ስኬት ተቋሙ የደረሰበት የላቀ የመከላከል አቅም ማሳያ መሆኑንም ጠቁመዋል።   በተቋሙ ለ44 ዓመታት በማገልገል የሕይወት ዘመን ተሸላሚ የሆኑት ጎንፋ አያና ተቋሙን ባገለገሉባቸው ዓመታት ኢንስቲትዩቱ የስምና አደረጃጀት ለውጥ በማድረግ በሕብረተሰብ ጤና ላይ ጉልህ ድርሻ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል። ኢንስቲትዩቱ አሁን ላይ የቴክኖሎጂና የባለሙያ አቅሙን በማሳደግ ተወዳዳሪ ተቋም መሆን መቻሉን ተናግረዋል። ለበርካታ ዓመታት በማገልገል እውቅና በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው፣ የአሁኑ ትውልድም ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ሀገሩን በተሻለ መንገድ እንዲያገለግል አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
የዲጂታል ሪፎርሙ በአዲስ አበባ የመሬት ዘርፍ ብልሹ አሰራርን በመቀነስ ገቢን አሳድጓል
Jul 18, 2026 137
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የተተገበረው የዲጂታል ሪፎርም የመሬት አገልግሎትን በማዘመን፣ ብልሹ አሰራርን በመቀነስና የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን በማጠናከር ውጤታማ ለውጥ ማምጣቱን የከተማው መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ኃላፊ መኮንን ያኢ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን ሪፎርም ተከትሎ በከተማው የመሬት አገልግሎትን ዘመናዊ፣ ግልጽና ከሰው ንክኪ የተላቀቀ ለማድረግ ሰፊ የለውጥ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በሪፎርሙ ማዕቀፍ ከ720 ሺህ በላይ የመሬት ማህደራት ስካን ተደርገው ወደ ዲጂታል መረጃ ቋት መግባታቸውን ገልጸው፤ የመረጃ ደህንነትን ከማጠናከር ባለፈ ህገ ወጥ የካርታ ዝግጅትና የመሬት ወረራ ወንጀሎችን ለመቀነስ አስተዋፅኦ አበርክቷል ብለዋል። በተጨማሪም የመሬት አገልግሎቶችን በኦንላይን ስርዓት በማቅረብ የአገልግሎት ፍጥነትን ከማሳደግ በተጨማሪ ለሙስናና ብልሹ አሰራር የነበረውን ተጋላጭነት በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን ገልጸዋል። በዘጠኝ ወራት ውስጥ 39 ሺህ የሚጠጉ ኢ-ካርታዎች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው፤ የይዞታ መረጃዎችም በዲጂታል ስርዓት እንዲመዘገቡና እንዲጠበቁ መደረጉን አመልክተዋል። በአስራ አንዱ ክፍለ ከተሞች ተበታትኖ የነበረውን የመሬት ቤዝማፕ ወደ አንድ ማዕከላዊ የመረጃ ቋት ማምጣት መቻሉንም ጨምረው አብራርተዋል። አቶ መኮንን እንዳሉት፤ ቢሮው በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ የተቀናጀ የመሬት መረጃ ስርዓት ወደ ስራ በማስገባት የሁለተኛ የመብት ፈጠራ፣ የካርታ ድርርቦሽና ሌሎች የማጭበርበር ሙከራዎችን ከመፈጸማቸው በፊት የሚለይና ለባለይዞታዎች ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ የቴክኖሎጂ አቅም ገንብቷል። በአዲስ መሶብ አገልግሎት ማዕከላት 14 የመሬት አገልግሎቶችን ወደ ዘመናዊ የአንድ ማዕከል ስርዓት በማስገባት በቀጣዮቹ 90 ቀናት በአስራ አንዱም ማዕከላት ሙሉ በሙሉ እንዲሰጡ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አሰራሩ የአገልግሎት መዘግየትን በመቀነስ ሙስናን ለመግታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት አመልክተዋል። የመሬት አገልግሎት ዲጂታላይዜሽን በገቢ አሰባሰብ ላይም ከፍተኛ ለውጥ ማምጣቱን ጠቁመው፤ ከአምስት ዓመታት በፊት ከአምስት ቢሊየን ብር ያልበለጠ የነበረው ከመሬትና ይዞታ የሚገኝ ገቢ በ2018 በጀት ዓመት 19 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መድረሱን ተናግረዋል። በመሬት ዘርፉ የሚፈጸሙ ህገ ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከልና ተጠያቂነትን ለማስፈን በርካታ አመራሮችና ሰራተኞች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸው፤ ይህም አገልግሎቱን ግልጽ፣ ተጠያቂና ለተገልጋዮች አስተማማኝ ለማድረግ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል።
ስፖርት
“ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ” ታላቁ ሩጫ በሐረር ከተማ ተካሄደ
Jul 19, 2026 115
ሀረር ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ “ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018” የ10 ኪሎ ሜትር ታላቁ ሩጫ ውድድር በሐረር ከተማ ተካሄደ። በውድድሩ በተለያየ የዕድሜ ክልል ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ አትሌቶች፣ ተጋባዥ እንግዶች፣ የውጪ አገር ቱሪስቶች፣ አርቲስቶችን ጨምሮ በርካታ ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል። ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ የሩጫ ውድድር ቀደም ሲል በደብረብርሃን፣ ሀዋሳ፣ ጅማ፣ አርባ ምንጭና በቆጂ ከተሞች የተካሄደ ሲሆን የፍጻሜ ውድድሩ ዛሬ በሐረር ከተማ ተካሂዷል።   በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ በተካሄደው የታላቁ ሩጫ ውድድርን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መክዩ መሀመድና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተው አስጀምረዋል። በ10 ኪሎ ሜትር በተካሄደው በዚህ ውድድር በወንዶች ሴና ገመቹ ሲያሸንፍ፤ ምህረት አወቀና ኢብራሂም መሀመድ በቅደም ተከተል 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል። በሴቶች ራሔል እምቢበል ስታሸንፍ አምረን ሸምሱና አዚዛ መሀመድ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን አግኝተዋል።   በሁለቱም ጾታ ከተደረገው የአትሌቶች ውድድር በተጨማሪ በአዋቂዎች፣ በወጣቶች፣ በታዳጊ ሕጻናትና በሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በሁለቱም ጾታዎች የ5 ኪሎ ሜትር ውድድር ተከሂዷል። ውድድሩን ላሸነፉ ተወዳዳሪዎች የተዘጋጀላቸውን የማበረታቻ ሽልማት ከእለቱ የክብር እንግዳ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መክዩ መሀመድ አበርክተዋል።   “ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018” ታላቁ ሩጫ ውድድር ቱሪዝም ሚኒስቴር እና ታላቁ ሩጫ በኢትዮዽያ በመተባበር ያዘጋጁት የጎዳና ላይ ውድድር መሆኑ ተገልጿል። ውድድሩ በሕዝቦች መካከል አብሮነትን የማጠናከር፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የማሳደግ እንዲሁም አዲስ የስፖርት መነቃቃትን የመፍጠር ዓላማ እንዳለውም ተመላክቷል።
አርጀንቲና የዓለም ዋንጫ ክብሯን ታስጠብቃለች ወይስ ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ዳግም አሸናፊ ትሆናለች?
Jul 19, 2026 274
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን እና አርጀንቲና ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ የዓለም አይኖች አርፈውበታል። ጨዋታው ምሽት አራት ሰዓት ላይ በኒው ዮርክ ኒው ጀርዚ ስታዲየም ይካሄዳል። ስፔን በግማሽ ፍጻሜው ለዋንጫ ታልፋለች ተብላ የተጠበቀችውን ፈረንሳይን 2 ለ 0 በመርታት በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ ለፍጻሜ ቀርባለች። የወቅቱ የዋንጫ ባለቤት አርጀንቲና እንግሊዝን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለተከታታይ ሁለት የዓለም ዋንጫዎች ለፍጻሜ ደርሳለች። አርጀንቲና ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስታልፍ የአሁኑ ለሰባተኛ ጊዜ ነው። ሁለቱ ሀገራት ከዚህ ቀደም በዓለም ዋንጫው አንድ ጊዜ ተገናኝተዋል። እንግሊዝ እ.አ.አ በ1966 ባዘጋጀችው ስምንተኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በምድብ ሁለት ተገናኝተው አርጀንቲና 2 ለ 1 አሸንፋለች። ሉዊስ አርቲም ለአርጀንቲና ሁለቱን ግቦች አስቆጥሯል። ፒሪ የስፔንን ጎል በወቅቱ ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ሀገራቱ በውድድር እና ወዳጅነት ጨዋታዎች 14 ጊዜ ተጫውተው በተመሳሳይ ስድስት ጊዜ ድል ቀንቷቸዋል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል። ስፔን በ14ቱ ጨዋታዎች ላይ 22 ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ አርጀንቲና 18 ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፋለች። እ.አ.አ በ2018 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 19ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ስፔን ብቸኛ ክብሯን ያገኘችበት ነው። ተጋጣሚዋ አርጀንቲና ከዚህ ቀደም ስድስት ጊዜ ለፍጻሜ ደርሳ ሶስቱን በማሸነፍ በውድድሩ ስኬታ ከሚባሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። አርጀንቲና የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈች ከጀርመን እና ጣልያን ጋር በተመሳሳይ አራት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያነሳች ሀገር ትሆናለች። በተጨማሪም የደቡብ አሜሪካ ሀገር ከጣልያን እና ብራዚል በመቀጠል ዓለም ዋንጫን በተከታታይ ያነሳች ሀገር ለመሆን ትጫወታለች። ሌላኛው ትኩረት የሳበው ጉዳይ ሀገራቱ የየአህጉራቸው ውድድሮች የወቅቱ አሸናፊ መሆናቸው ነው። ስፔን የአውሮፓ ዋንጫ፣ አርጀንቲና የኮፓ አሜሪካ አሸናፊ ናቸው። የአውሮፓ እና የደቡብ አሜሪካ ቁንጮዎች የሚያደርጉት ፍልሚያ ትኩረትን ስቧል። አውሮፓዊቷ ስፔን እ.አ.አ በ2010 የዓለም ዋንጫን ከማንሳቷ በፊት የ2008 የአውሮፓ ዋንጫ አሸናፊ ነበረች። ስፔን የወቅቱ የአውሮፓ ዋንጫ ባለቤት ሆና ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ መቅረቧ ገጠመኙን የተለየ አድርጎታል። በዘንድሮው ዓለም ዋንጫ ድንቅ ብቃቱን እያሳየ የሚገኘው ሊዮኔል ሜሲ በዛሬው ጨዋታ ልዩ ትኩረት አግኝቷል። የ39 ዓመቱ ሜሲ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ስምንት ጎሎችን በማስቆጠር እና አራት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል ከኪሊያን እምባፔ (10 ጎሎች ሲያስቆጥር እና አራት የግብ እድሎችን ፈጥሯል) በኮከብ ግብ አግቢነቱ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በዓለም ዋንጫው 21 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ በምንጊዜውም የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ዝርዝር ውስጥ በእምባፔ አንድ ጎል ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ሜሲ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ለማጠናቀቅ እና የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን መሪነት ይዞ ለመቀጠል ሁለት ግቦችን ማስቆጠር እና ለግብ የሚሆን ኳስ ማቀበል ይጠበቅበታል። አርጀንቲናዊው ኮከብ በዓለም ዋንጫ በርካታ ጨዋታዎችን በማድረግ (33) እና በርካታ ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል (12) የክብረ ወሰን ባለቤት ነው። እድሜው በገፋበት ሰዓት እያሳየ ያለው ብቃት አድናቆት እንዲጎርፍለት አድርጓል። በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አንድ ግብ ያስቆጠረው የ18 ዓመቱ ላሚን ያማል ከስፔን በኩል ትኩረት የተሰጠው ተጫዋች ነው። ስፔን በጨዋታው ላይ የኳስ ቁጥጥርን መሰረት ያደረገ እና የክንፍ መስመር የማጥቃት እንቅሰቃሴ ላይ ያተኮረ የአጨዋወት ስልት ወደ ሜዳ ይዛ ትገባለች ተብሎ ይጠበቃል። ተጋጣሚዋ አርጀንቲና የተደራጀ የመከላከል ቅርጽ በመያዝ ኳስ ሲያገኙ በፈጣን መልሶ ማጥቃት ግብ የማስቆጠር አጨዋወትን ትከተላለች ተብሎ ይጠበቃል። ጨዋታው ጠንካራ እና በታክቲክ የታጠረ እንደሚሆን ይጠበቃል። የ46 ዓመቱ ስሎቬኒያዊ ስላቫኮ ቪንቺች ተጠባቂውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመሩታል። አሸናፊው ሀገር ከዋንጫው በተጨማሪ የ50 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ያገኛል። ሁለተኛ የሚወጣው ቡድን የ33 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይበረከትለታል። የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) አጠቃላይ በውድድሩ ላይ ለተሳተፉ ሀገራት የ871 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት አዘጋጅቷል።   አሜሪካዊው ዝነኛ ድምጻዊና ራፐር ፖስት ማሎን (Post Malone) የዓለም ዋንጫው የመዝጊያ ስነ ስርዓት ዋና አቅራቢ (Headline Performer) ነው። ከእሱ በተጨማሪ ሮቢ ዊሊያምስ፣ ኒኮል ሸርዚንገር እና ላውራ ፓውሲኒ የተባሉ ታዋቂ ድምጻውያን እንዲሁም ታዋቂው ዩቲዩበር አይሾው ስፒድ (IShowSpeed) በዝግጅቱ ላይ የሚሳተፉ ሲሆን፣ የሆሊውድ ተዋናዩ ቶም ክሩዝም ልዩ እንግዳ ሆኖ ይቀርባል። በእረፍት ሰዓት (Halftime Show) ላይ ደግሞ ማዶና፣ ሻኪራ፣ ጀስቲን ቢበር፣ ቢቲኤስ (BTS) እና በርና ቦይ ከኮልድ ፕለይ (Coldplay) ጋር በመሆን በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚቀርበው የእረፍት ሰዓት ትዕይንት ላይ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ። በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጣምራ አዘጋጅነት ከሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ ሲካሄድ የቆየው 23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ዛሬ ፍጻሜውን ያገኛል።
እንግሊዝ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቀቅ ኪሊያን ምባፔ አዲስ የዓለም ዋንጫ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል
Jul 19, 2026 329
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018 (ኢዜአ)፦ 10 ጎሎች በተቆጠሩበት የ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የደረጃ ጨዋታ እንግሊዝ ፈረንሳይን 6 ለ 4 አሸንፋለች። ከእኩለ ሌሊት በኋላ በሚያሚ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቡካዮ ሳካ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። ሳካ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ሀትሪክ የሰራ አራተኛው ተጫዋች ሆኗል። ዴክላን ራይስ ኢዝሪ ኮንሳ እና ጁድ ቤሊንግሃም ቀሪዎቹን ጎሎች ለሶስቱ አናብስቶች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኪሊያን ምባፔ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ብራድሊ ብራኮላ እና ኡስማን ዴምቤሌ ቀዎቹን ጎሎች ለሰማያዊዎቹ አስቆጥረዋል። እንግሊዝ በመጀመሪያው አጋማሽ፣ ፈረንሳይ በሁለተኛው አጋማሽ ብልጫ ወስደዋል። በመጀመሪያ አጋማሽ እንግሊዝ 4 ለ 0 እየመራች ብትወጣም ፈረንሳይ ከእረፍት መልስ አራት ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፋለች። ፈረንሳይ ልታሻንፋባቸው የምትችልባቸውን የግብ እድሎች አምክናለች። ጨዋታው በማጥቃት የታጀበ መሆኑንና የቡድኖቹ የላላ የመከላከል እንቅስቃሴ በርካታ ግቦች እንዲቆጠሩ አድርጓል። ጨዋታው አስገራሚ እንቅስቃሴ ተደርጎበታል። የሁለቱ ቡድኖች መርሐ ግብር በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ በርካታ ግቦች የተቆጠሩበት ጨዋታ ሆኗል። በዓለም ዋንጫ የደረጃ ጨዋታ ታሪክ በርካታ ግቦች የተቆጠሩበትም ሆኗል። የ27 ዓመቱ ኪሊያን እምባፔ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ወደ 10 ከፍ በማድረግ የኮከብ አስቆጣሪነቱን መምራት ጀምሯል። ለግብ አመቻችቶ ያቀበላቸውን ኳሶች ብዛት አራት አድርሷል። ከአርጀንቲናዊው ሊዮኔል ሜሲ ጋር ያለውን የግብ ልዩነት ወደ ሁለት ከፍ በማድረግ የወርቅ ጫማውን የመውሰድ እድሉን አስፍቷል። በተጨማሪም በአጠቃላይ በዓለም ዋንጫ ያስቆጠራቸውን ጎሎች 22 በማድረስ የምንጊዜም ከፍተኛ አስቆጣሪነቱን ከሜሲ (21) ተረክቧል። ለሀገሩ 66 ጎሎችን አስቆጥሯል። የፈረንሳዩ ማይክል ኦሊሴ በአንድ የዓለም ዋንጫ ሰባት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል የፔሌን (ስድስት የግብ እድል የመፍጠር) ክብረ ወሰንን ሰብሯል። የ23 ዓመቱ ጁድ ቤሊንግሃም በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ሰባት ጎሎችን በማስቆጠር በውድድሩ በአንድ የዓለም ዋንጫ በርካታ ግቦችን ያስቆጠረ እንግሊዛዊ ተጫዋች ሆኗል። ውጤቱን ተከትሎ እንግሊዝ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች። እንግሊዝ እ.አ.አ በ1966 አዘጋጅታ ራሷ ካስቀረችው ስምንተኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በኋላ በውድድሩ የተሻለ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ለዋንጫ የተጠበቀችው ፈረንሳይ አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የሁለት ጊዜ ዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ፈረንሳይ አራተኛ ሆኖ ማጠናቀቅ ያልተጠበቀ ሆኗል። ለ14 ዓመት የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን ያሰለጠኑት የ57 ዓመቱ ዲዲየር ዴሾ የመጨረሻ ጨዋታቸውን አድርገዋል። ዴሾ በ187 ጨዋታዎች ፈረንሳይ የመሩ ሲሆን አንድ ጊዜ የዓለም ዋንጫን አንስተዋል። ቡድኑን ለሶስት ተከታታይ ዓለም ዋንጫዎች ለፍጻሜ ያበቁ ስኬታማ አሰልጣኝም ናቸው። ዚነዲን ዚዳን በቀጣይ ቡድኑን በአሰልጣኝነት ይረከባል።
በአዲስ አበባ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ታዳጊዎች የክረምት ወራትን በክህሎት ማጎልበቻ እንዲያሳልፉ ዕድል ፈጥረዋል
Jul 18, 2026 196
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች የክረምት ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም ተሰጥኦዋቸውን ለማዳበር ትልቅ እድል እንደፈጠረላቸው ታዳጊዎች ገለጹ። መንግስት ለስፖርት ልማት ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በየደረጃው በመገንባት ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡ በአዲስ አበባ ብቁና ተወዳዳሪ ስፖርተኞችን ማፍራት የሚያስችሉ ውጤታማ የስፖርት ማዕከላትና የማዘውተሪያ ስፍራዎች ተገንብተዋል።   በተገነቡት ከ2ሺህ 580 በላይ የስፖርት ማዘውተሪያና ማሰልጠኛ ማዕከላት ብቃት ያላቸውን ታዳጊ ስፖርተኞች ማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑም ተመላክቷል፡፡ እነኚህ ዘመናዊና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የምታስተናግድበት አቅም መፍጠራቸውም ተገልጿል፡፡ በመዲናዋ በርካታ የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች መስፋፋታቸው ወጣቶችና ታዳጊዎች በተሻለ ስብዕና እንዲገነቡ የሚያስችሉ ብሎም አልባሌ ቦታዎች ከመዋል የታደጉ ናቸው፡፡ ኢዜአ በአዲስ አበባ በተገነቡ የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው ታዳጊዎች ከዚህ ቀደም በአካባቢያቸው ምቹ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ባለመኖራቸው ለስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ይቸገሩ እንደነበር ይናገራሉ። ታዳጊ እያብ ገብረስላሴ እንደሚለው፣ ቀደም ሲል በአካባቢው የነበሩት ሜዳዎች ለስፖርት እንቅስቃሴ አመቺ ስላልነበሩ ተሰጥዖውን ለማዳበር ተቸግሮ እንደነበር ይናገራል። አሁን ላይ በመዲናዋ በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡት ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ ታዳጊዎች ተሰጧቸውን በነፃነት የሚያዳብሩበትና ብቃታቸውን የሚያሳድጉበት ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን ይገልጻል።   ታዳጊ አብርሃም ታረቀኝ እና አማኑኤል ተስፋ በበኩላቸው፣ ቀደም ሲል የነበሩት ሜዳዎች ለጉዳት ይዳርጉ እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ግን መንግስት ምቹ ሜዳዎችን በመገንባቱ ያለምንም ስጋት በመለማመድ አቅማቸውን እየገነቡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።   ሜዳዎቹ በክረምትም ሆነ በበጋ እንዲሁም ምሽትን ጨምሮ አገልግሎት የሚሰጡ በመሆናቸው ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ ትልቅ ሚና እንዳላቸውም ተናግረዋል፡፡ የታዳጊዎች አሰልጣኝ የሆኑት ዮናስ እስክንድር፣ በመዲናዋ የተገነቡት የስፖርት ማዘውተሪያዎች ለታዳጊዎች የመዝናኛና የክህሎት ማሳደጊያ ምቹ መድረክ መሆናቸውን ገልጸዋል።   በተለይም በክረምት ወራት ተማሪዎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ በማስቻል፣ በስፖርት የታነጸ ጤናማ ትውልድ ለመቅረጽ ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው አስረድተዋል። የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የስፖርት ስልጠና ዳይሬክተር ጎሳዬ አለማየው፣ መንግስት ባለፉት ዓመታት የስፖርት ዘርፉን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ማከናወኑን አስታውቀዋል። በመዲናዋ በተገነቡት ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያዎች አማካኝነትም፣ ታዳጊዎች ክህሎታቸውን አዳብረው በስፖርት የታነጹ እንዲሆኑ ትልቅ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   በዘንድሮ የክረምት ወራት ከ67 ሺህ በላይ ታዳጊዎችን በበጎ ፈቃድ በማሰልጠን ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና መሰረታዊ የስፖርት ክህሎት እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። በስልጠናው ወቅት ከፍተኛ ክህሎት ያሳዩ ታዳጊዎች ወደ በጋው የታዳጊ ወጣት መርሃ ግብር እንዲቀላቀሉ እንደሚደረግ ጨምረው ተናግረዋል።
አካባቢ ጥበቃ
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ከመቋቋም ባለፈ የወጣቶችን የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ባህል አሳድጓል
Jul 18, 2026 603
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ከመቋቋም ባለፈ የወጣቶችን የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ባህል እያሳደገ መሆኑን የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ገለጸ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብር የደን መመናመንና የአፈር መሸርሸርን በመከላከል በኩል አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።   ባለፉት ዓመታት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በዘንድሮው ዓመትም 'ተስፋን እንትከል' በሚል መሪ ሐሳብ ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡ መርሃግብሩ የሀገሪቱን የደንና የአረንጓዴ ሽፋን ከማሳደጉ ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር አስችሏል። የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ከከተማ አስተዳደሩ የከተማ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት አካሂዷል። በመርሃ-ግብሩ የተሳተፉ ኃላፊዎችና ወጣቶች የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ፣ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ባህልን ለማሳደግ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን ገልፀዋል። የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ፎሊ ንጉሴ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም፣ የከተማዋን ውበት ለመጠበቅና ምቹ አካባቢን ለመፍጠር አስተዋፅኦ እንዳለው ተናግራለች። ችግኝ ከመትከል ባለፈ በዘላቂነት መንከባከብና መጠበቅ እንደሚገባም ገልፃለች። የማህበሩ ዋና ጸሐፊ ኤርሚያስ ወንድሙ በበኩሉ፣ የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከተበሰረበት ጊዜ አንስቶ ወጣቱ በንቃት እየተሳተፈ እንደሚገኝ ተናግሯል።   መርሃ-ግብሩ ለተተኪው ትውልድ የተሻለች፣ በልምላሜና በተስፋ የተሞላች ሀገር ማስረከብ የሚያስችል መሆኑንም ገልጿል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ከተማዋን አረንጓዴ፣ ፅዱና ምቹ ስነ-ምህዳር እንድትላበስ አስችሏል ያሉት ደግሞ የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ የጽዳትና ውበት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የኑስ መሐመድ ናቸው።   በመርሃግብሩ የተሳተፉት ወጣት ከተማ ባልቻና ወጣት ተገኑ ቦነ በበኩላቸው ዛሬ ችግኞችን መንከባከብ ለመጪው ትውልድ ዐሻራን ማኖር በመሆኑ ችግኞችን በዘላቂነት እንደሚንከባከቡ ተናግረዋል።  
የጭስ አልባ ትራንስፖርት ዘርፍን ለማስፋፋት ከዓለም ባንክ ጋር በአጋርነት ለመሥራት ተስማምተናል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jul 17, 2026 342
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማን የትራንስፖርት አገልግሎት ይበልጥ ለማሻሻል ከዓለም ባንክ ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ዳይሬክተር ከሆኑት ማርያም ሳሊም ጋር ባደረጉት ውይይት፣ ከተማ አስተዳደሩ የትራንስፖርት ዘርፉን ለማዘመን እና በተለይም የጭስ አልባ ትራንስፖርት (E-mobility) ተደራሽነትን በስፋት ለማዳረስ እያከናወነ ባለው ሥራ ዙሪያ በዝርዝር መምከራቸውን ገልጸዋል።   በውይይታቸውም አስተዳደሩ የጀመራቸውን ሥራዎች ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ጠቁመዋል። እንዲሁም በዘርፉ የተሰማሩ የግል ተቋማትን ለመደገፍ ከዓለም ባንክ ጋር በአጋርነት እና በትብብር በጋራ ለመሥራት ተግባብተናል ብለዋል።   ከንቲባ አዳነች ለዳይሬክተሯ ማርያም ሳሊም እና አብረዋቸው ለነበሩት የቴክኒካል ቡድን አባላት በራሳቸው እና በአዲስ አበባ ሕዝብ ስም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በምዕራብ ሸዋ ዞን በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከ8 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በፍራፍሬ እየለማ ነው
Jul 16, 2026 442
አምቦ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦በምዕራብ ሸዋ ዞን በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 8 ሺህ 463 ሄክታር መሬት የሚሸፍን የፍራፍሬ ልማት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በምዕራብ ሸዋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት የደን ልማት ባለሙያ አቶ ጉደታ ጡር ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተያዘው ክረምት ከ15 ሚሊዮን በላይ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ችግኞች ተዘጋጅተው እየተተከሉ ይገኛሉ።   የሚተከሉት የፍራፍሬ ችግኞች በአካባቢው የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ማኅበረሰቡ ተጨማሪ ገቢ በማግኘት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱን እንዲያሳድግ ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸውም ገልጸዋል። በመርሐ ግብሩ ከተዘጋጁት የፍራፍሬ ዝርያዎች መካከል ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ሙዝ እና አፕል እንደሚገኙበትም ባለሙያው ጠቁመዋል። በልማት ሥራው ዙሪያ ለአርሶ አደሮቹ ሥልጠና መሰጠቱን የጠቀሱት አቶ ጉደታ፤ በአሁኑ ወቅትም አስፈላጊው ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ አስረድተዋል። በዞኑ በክረምቱ ወቅት በአጠቃላይ በ8 ሺህ 463 ሄክታር መሬት ላይ የፍራፍሬ ችግኝ ተከላ እየተካሄደ መሆኑንና በዚህ የልማት ሥራ ላይ 131 ሺህ 576 አርሶ አደሮች በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙም አስታውቀዋል።   በዞኑ የሚገኙ አርሶ አደሮች ከመደበኛ የግብርና ሥራቸው በተጓዳኝ በፍራፍሬ ልማት ላይ በመሰማራታቸው ተጨማሪ ገቢ ማግኘት መቻላቸውን ጠቅሰዋል። ከዚህም በተጨማሪ ባለፉት ዓመታት የተተከሉ የፍራፍሬ ችግኞች የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና የደረቁ ምንጮች እንዲያንሰራሩ በማድረጋቸው፣ የአርሶ አደሮቹን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን አክለዋል። በምዕራብ ሸዋ ዞን በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እስካሁን ከ11 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በፍራፍሬ ልማት መሸፈኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ ለአረንጓዴ ልማት ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር አሳይታለች
Jul 16, 2026 352
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ ለአረንጓዴ ልማት ያላትን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ማሳየቷን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ፀጋ ገለጹ። በኢትዮጵያ የአረንጓዴ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ማጠናከር ላይ ለተቀረጸው የምርምር ፕሮጀክት የተዘጋጀ የማስጀመሪያ አውደ ጥናት እየተካሄደ ይገኛል።   በአውደ ጥናቱ መክፈቻ ላይ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ ፀጋ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ ለአረንጓዴ ልማት ያላትን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር አሳይታለች። ይህም በታዳሽ ኃይል መስፋፋት፣ በዘላቂ ግብርና እና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ በሆኑ የኢንዱስትሪ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በግልጽ ይንጸባረቃል ብለዋል። አረንጓዴ ኢኮኖሚን መገንባት የመንግሥትን ጥረት ብቻ ሳይሆን የሁሉንም አካላት ንቁ ተሳትፎ እንደሚጠይቅም አንስተዋል። በተለይም አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ማሳተፍ ወሳኝና አማራጭ የሌለው ተግባር መሆኑን ገልጸው፤ እነዚህ ኢንተርፕራይዞች ለኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለእሴት ሰንሰለት ዕድገት፣ ለሀገር ውስጥ ምርት እንዲሁም ለኢኮኖሚ ብዝኃነት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አስገንዝበዋል። እነዚህ ኢንተርፕራይዞች ለኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለእሴት ሰንሰለት ዕድገት፣ ለሀገር ውስጥ ምርት እንዲሁም ለኢኮኖሚ ብዝኃነት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አስገንዝበዋል። ወደ አረንጓዴ ማኑፋክቸሪንግ የሚደረገው ሽግግር የመንግስት፣ የግልና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ አካሄድ ያስፈልጋል ብለዋል። በኢንስቲትዩቱ በአምራች ዘርፍ የማዕድን ዘርፍ ክፍል ኃላፊ እና መሪ ተመራማሪ ነጻነት ጆቴ (ዶ/ር)፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ አካባቢን የማይበክልና ዘላቂ የምርት ሥርዓት መገንባት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።   በኢትዮጵያ የሚገኙ የአረንጓዴ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን የሚዳስስ ጥናት እንደሚደረግ ነው የገለጹት። የጥናቱ ዋና ዓላማ የኢንተርፕራይዞቹን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ዕድሎችና ፈተናዎች በማመላከት ተወዳዳሪነታቸውን ማሳደግ ነው ብለዋል። በአፍሪካ ክላይሜት ፋውንዴሽን የፕሮጀክት ማናጀር ሳህሌ ታምሩ፤ ፋውንዴሽኑ በታዳሽ ኃይል፣ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ፣ የትራንስፖርትና የፋይናንስ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ጥናቶችና ምርምሮችን እየደገፈ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።   ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በዓለም አቀፍ ገበያ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ተወዳዳሪነቷንና ተጠቃሚነቷን ለማሳደግ ጥናቱ አስተዋጽኦ የሚያደርግ በመሆኑ በጋራ እንሰራለን ብለዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 20066
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 12999
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 11794
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 11691
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው።   የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
ክልሎችን በወፍ በረር
Jul 19, 2026 73
ሀምሌ ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ክልሎችን በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? 👉አማራ ክልል የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ። ለ30 ዓመታት ያህል ተቋርጦ የነበረው የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ በዘመናዊ መልክ ተገንብቶ በይፋ ተመርቋል። አወሮፕላን ማረፊያው 2 ሺህ 400 ሜትር ርዝመትና 30 ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን፣ እንደ Q400 እና B737 ያሉ ግዙፍ የሕዝብና የጭነት አውሮፕላኖችን ማሳረፍ ይችላል። ይህም የአካባቢውን ንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ያነቃቃል ተብሏል። በምርቃ መርሃ ግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፌዴራል እና የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ታድመዋል። 👉ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል "ትምህርት ለልጄ" የክረምት ንቅናቄ መካሄድ። በትምህርት ቤቶች ደረጃንና የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ያለመ የ2018 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ንቅናቄ መድረክ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ ተካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተማሪዎች ብቁ ሆነው እንዲወጡ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻልና ግብዓት በማሟላት ረገድ በትኩረት መሠራቱን ገልጸዋል። 👉ድሬዳዋ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲዎችን በትክክለኛ መረጃ ላይ መስርቶ ለመቅረጽ የሚያስችል የዲጂታል ሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ሥርዓት በድሬዳዋ ተጀምሯል። ተግባሩ የተከናወነው በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት እና በኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ሲሆን የተቋማቱ ዋና ዳይሬክተሮች ሰላማዊት ዳዊት እና ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ይህ ሥርዓት የ"ዲጂታል 2030" ትግበራ አካል ነው። 👉ሶማሌ ክልል ሰብዓዊ መብትና ሰላም ግንባታ ጉዞ። ‘ሰብዓዊ መብትና የሰላም ግንባታ’ በሚል መሪ ሐሳብ አገር አቀፍ የጸጥታና ፍትሕ አካላት ጉባኤ በጅግጅጋ ከተማ ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ የተጠርጣሪዎችና የታራሚዎች አያያዝ መሻሻል ማሳየቱን የጠቀሱ ሲሆን፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድ በበኩላቸው በክልሉ ለሰላም፣ ለጸጥታና ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። 👉ሲዳማ ክልል የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ስኬት- የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ (CBE) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና ከ20 ዓመት በታች ውድድር አሸናፊ ለሆነው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ በየነ በራሳ የክለቡ ውጤት የአንድነትና የትጋት ማሳያ መሆኑን ገልጸው፣ ይህንን ስኬት በአርአያነት በመውሰድ በሌሎች የልማት መስኮችም መድገም እንደሚገባ አሳስበዋል። 👉ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የበጀት ዓመት ግምገማ። የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን እምቅ አቅሞችን በማልማት በሁሉም ዘርፎች የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መቻሉንና በቀጣይም አገራዊ ኢኒሼቲቮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። በተመሳሳይ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ በተፈጠረው "ንጋት ሐይቅ" ከተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ 10 ሺህ 799 ቶን ዓሳ ማምረት መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ኢትቻ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። 👉አፋር ክልል የገቢ አሰባሰብ ውጤት። በበጀት ዓመቱ ከ8 ቢሊዮን 524 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ አወል አብዱ ገልጸዋል። ለውጤቱ መገኘት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር መዘርጋቱ፣ የግብር ከፋዩ ግንዛቤ ማደግና የአመራሩ ቁርጠኝነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። 👉ሐረሪ ክልል የበጀት አፈጻጸምና የ2019 በጀት መጽደቅ። የ2018 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ አካላት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። ምክር ቤቱ የልማት ዕቅዶችን ለማሳካት ለ2019 በጀት ዓመት 12 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በጀት አጽድቋል። ከበጀቱ ውስጥ ከፍተኛው ድርሻ ለካፒታል በጀት የተመደበ ሲሆን፣ ትኩረቱም ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ነው። 👉ኦሮሚያ ክልል የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሂደት። በ2018 በጀት ዓመት የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ የልማት ዕድሎችን፣ የሰው ኃይልንና ዕውቀትን አቀናጅቶ በመምራት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። በቀጣይም የተመዘገቡ ድሎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ከመደመር እሳቤ የተቀዱ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች በላቀ ቁርጠኝነትና በሕዝብ ተሳትፎ መመራት እንዳለባቸው የሥራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። 👉ደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ከ150 ሚሊዮን 250 ሺህ ብር በላይ ከምዝበራ ማዳንና በኦዲት ግኝት ማስመለስ መቻሉን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ አስታውቀዋል። ከዚህ ውስጥ 68.6 ሚሊዮን ብሩ በአስቸኳይ ሙስና መከላከል ሥራ ከምዝበራ የዳነ ነው። ከገንዘብ በተጨማሪ 14 ሺህ 673 ካሬ ሜትር የከተማ መሬት እና 645 ሄክታር የገጠር መሬት፣ እንዲሁም በርካታ የመንግሥትና የሕዝብ ሀብቶችን ማዳንና ማስመለስ ተችሏል። የአገልግሎት አፈጻጸሙን በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል ቅንጅታዊ አሠራርን ማሳደግ እንደሚገባም ተገልጿል።
ኢትዮጵያ፤ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የዕውቀት፣ የሰላምና የልማት ድልድይ!!
Jul 16, 2026 497
ድንበር ያልገደበው ትስስር ኢትዮጵያ፤ የኢትዮጵያ ቀጣናዊ የዕውቀት፣ የሰላምና የልማት ድልድይ!! በቤተልሔም ባህሩ የሀገራት ድንበር በካርታ ላይ የተሳሉ መስመሮች ናቸው። በሰዎች ሕይወት ውስጥ ግን አንዳንድ ጊዜ ወንድማማችነትን የሚያሳድጉ ድልድዮች ይሆናሉ። በደቡብ ሱዳንና በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ ያደገው ኒክሰን አንቶኒ ድንበርን የሚያውቀው እንደ መለያ መስመር ሳይሆን፣ እንደ መገናኛ መስመር ነው።   በልጅነቱም በድንበር አካባቢ ባሉ መንደሮች መካከል የሚኖረውን የገበያ ትስስር፣ የባህል መመሳሰል፣ የቋንቋ መቀራረብና ከሁሉም በላይ የሰዎች ተፈጥሯዊ መተማመን እየተመለከተ አድጓል። ስለዚህም ኢትዮጵያ በእርሱ አዕምሮ ውስጥ ከጎረቤት ሀገርነት ይልቅ የሁለተኛ ቤት ስሜት የፈጠረች ሀገር ሆናለች። ጥቁር አንበሳ፤ ከሆስፒታል በላይ የቀጣናውና የአፍሪካ የእውቀት ማዕከል ያ የልጅነት ትዝታ ግን አንድ ቀን የሕይወቱን መስመር የሚቀይስበት አጋጣሚ እንደሚፈጠር አላሰበም ነበር። ዛሬ ዶክተር ኒክሰን አንቶኒ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሕፃናት ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊቲ ትምህርቱን እየተከታተለ ይገኛል። በልጅነቱ በድንበር አካባቢ ያየው ወንድማማችነት ዛሬ ላይ በዕውቀትና በሕይወት ማዳን ሙያ እየታነጸ ይገኛል። በልጅነቱ በድንበር ላይ የተመለከተው የሕዝቦች ወንድማማችነት ዛሬ በእጆቹ ውስጥ ሕይወትን የሚያድን ሙያ ሆኗል። ይህ የአንድ ሰው የሙያ ስኬት ብቻ አይደለም፤ ሀገራት በእምነት ሲተባበሩ የሚፈጠረው የሰው ታሪክ ነው። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ የምትሰጠው ትምህርት ዲግሪ ብቻ አይደለም፤ ኃላፊነትም ጭምር ነው። ዛሬ በአዲስ አበባ የሚማረው ሐኪም ነገ በጁባ፣ በኪጋሊ ወይም በሞቃዲሾ ውስጥ የሺዎችን ሕይወት ሊታደግ ይችላል። ስለዚህ ዛሬ በክፍል ውስጥ የሚሰጥ አንድ ትምህርት ነገ በሌላ ሀገር የሚድን አንድ ሕፃን ሕይወት ሊሆን ይችላል። ይህም ነው በትብብር ላይ የተመሠረተ የሰው ኃይል ልማት የሚሰኘው ቃል፣ ከፖሊሲ ሰነድ ወጥቶ ሕይወት የሚያገኘው። ነግቶ ሲጠባ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ኮሪደሮች ውስጥ ነጭ ጋውን የለበሱ ወጣት ሐኪሞች በፍጥነት ሲመላለሱ ይታያሉ። ከሩቅ ለሚመለከታቸው ሰው ማን ኢትዮጵያዊ፣ ማን ደቡብ ሱዳናዊ ወይም ማን ሩዋንዳዊ እንደሆነ መለየት ያዳግታል። ሁሉም አንድ ቋንቋ ይናገራሉ—የሕክምናን። ሁሉም አንድ ዓላማ አላቸው—ሕይወትን ማዳን። ይህ ምስል ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና እየገነባች ያለውን አዲስ የትብብር ምዕራፍ በደማቅ ቀለም አጉልቶ ያሳያል። ዛሬ በኢትዮጵያ በሚገኙ 19 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ከ430 በላይ ከጎረቤት ሀገራት የመጡ ሐኪሞች በነፃ የስፔሻሊቲና የሰብ-ስፔሻሊቲ ስልጠና በመከታተል ላይ ናቸው። በዚህ መርሃ ግብር የተመረቁ 105 ሐኪሞችም ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ሕዝባቸውን እያገለገሉ ነው። እነዚህ ቁጥሮች በራሳቸው ግን ሙሉ ታሪኩን አይነግሩም። ታሪኩ የሚጀምረው እንደ ኒክሰን ባሉ ወጣቶች ዐይን ውስጥ ከሚነበበው ተስፋ ነው። "ይህ ዕድል ለእኔ ትምህርት ብቻ አይደለም፤ ወደ ሀገሬ ተመልሼ ልጆችን የማድንበት ተልዕኮ ነው" ይላል። ያገኘው ልምድ የደቡብ ሱዳንን እንዲሁም የቀጣናውን አጠቃላይ የጤና ሥርዓት በጋራ ለማጠናከር እንደሚረዳ ያብራራል። ይህም የአንድ ወጣት ሐኪም ሃሳብ ብቻ አይደለም፤ የቀጣናው የጋራ የወደፊት ርዕይም ጭምር ነው። የዶክተር ኒክሰን ታሪክ ብቻውን አይቆምም። በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መማሪያ ክፍሎችና በቀዶ ሕክምና ክፍሎች ውስጥ የሚገኙ በርካታ ወጣት ሐኪሞች በየራሳቸው የተለያየ ታሪክ ቢኖራቸውም፣ የሚያገናኛቸው አንድ የጋራ ዕሴት አለ። እርሱም ኢትዮጵያ የዕውቀት ዲፕሎማሲ ማዕከል መሆኗን ነው። በአፍሪካ ታሪክ የሀገራት ግንኙነት ብዙ ጊዜ የሚገለጸው በፖለቲካ፣ በድንበር ወይም በደኅንነት መነፅር መሆኑን የታሪክ ድርሳናት ያስረግጣሉ። ዛሬ ግን አዲስ ታሪክ በመፃፍ ላይ ይገኛል። የዚህ ታሪክ ቋንቋ የጦር መሣሪያ ሳይሆን የሕክምና አገልግሎት ነው፤ የጦር ሜዳ ሳይሆን የቀዶ ሕክምና ክፍል ነው፤ የፉክክር ምልክት ሳይሆን የጋራ ዕውቀት ነው።   ይህንን እውነታ የሚያሳይ ሌላ ምሳሌ ደግሞ ደቡብ ሱዳናዊው ዶክተር ሲስቶ ዶሚኒክ ነው። በኢትዮጵያ የኦርቶፔዲክና ትራኦማ ቀዶ ሕክምና ስልጠና እየተከታተለ የሚገኘው ይህ ወጣት፣ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ የተቀበለው የእንግዳ ተቀባይነት ባህል ከሙያው በላይ የሰው ልጅን ሰብዓዊ ክብር በጉልህ እንደሚያንጸባርቅ ይናገራል። "ሌሎች ሀገራት ሄጄ ተምሬያለሁ፤ ኢትዮጵያ ስመጣ ግን እንደ እንግዳ አልተሰማኝም። እንደ ቤቴ ነበር የተሰማኝ፤ እየኖርኩ ያለሁትም እንደዚያ ነው" የሚለው ንግግሩ ከአንድ ግለሰብ ልምድ በላይ ነው። ይህም የሀገራቱን ሕዝቦች ለዘመናት የተገነባ መተማመን የሚገጥ ማስረጃ ነው። ዶክተር ሲስቶ ወደ ደቡብ ሱዳን ሲመለስ የሚያክመው የሀገሩን ዜጎች ብቻ አይሆንም፤ በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም የእርሱ ታካሚዎች ይሆናሉ። በዚህ መልኩ በአንድ የቀዶ ሕክምና ክፍል የተገኘ ዕውቀት ድንበርን ተሻግሮ ሌላ ሀገር ውስጥ ሕይወት ያድናል። ይህ ደግሞ የዕውቀት ዲፕሎማሲ በተግባር ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ሕያው ምስል ነው። ከኪጋሊ የተጀመረ ሕልም፤ በአዲስ አበባ የዘለቀ የመሻት ስኬት የሩዋንዳዊው ዶክተር ሙሂር ፍራንክ ታሪክ ደግሞ ሌላ የቀጣናዊ ትብብር ገጽን ያሳያል። በኪጋሊ ሆስፒታሎች ውስጥ በትጋት የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ሐኪሞችን ሲመለከት ያደገው ይህ ወጣት፣ በፊታቸው ላይ ያየው ሙያዊ ብቃትና ርህራሄ አንድ ቀን እርሱንም ወደ አዲስ አበባ እንደሚያመጣው አስቦ አያውቅም። ዛሬ ግን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኒውሮ ሰርጀሪ ስፔሻሊቲ ተማሪ ነው። ለእርሱ ኢትዮጵያ የትምህርት መዳረሻ ብቻ አይደለችም፤ በሩዋንዳ የሚያልመውን የጤና ሥርዓት የሚገነባበት ሁለተኛ ቤቱና የዕውቀት መሠረት ጭምር ነው። ሩዋንዳ በጤና ዘርፍ ያላትን የሰው ኃይል በፍጥነት ለማሳደግ በተያዘው ብሔራዊ ዕቅድ ውስጥ፣ በኢትዮጵያ የሚሰጠው ስልጠና የሚያበረክተው ሚና ትልቅ መሆኑን ይገልጻል።   እንደ ወጣቱ ዶክተር ገለፃም ''ይህ የሚያሳየው አንድ እውነት አለ፤ አንድ ሀገር የሌላውን ሀገር የሰው ኃይል ሲያጠናክር፣ በእውነቱ የጋራ የቀጣናውን መጪ ጊዜ እየገነባ መሆኑን ነው የሚያስገነዝበው'' ይላል። በጤና ሚኒስቴር የጤና ዘርፍ ሰው ኃይል ልማት ማሻሻያ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሰግድ ሳሙኤል በበኩላቸው፣ ባለፉት ስድስት ዓመታት ሲሰጥ በቆየው ነፃ የሕክምና ስልጠና ዕድል እጅግ ውጤታማ እንደነበር ይገልጻሉ። ይህ ትብብርና አጋርነት በቀጣናው ሀገራት የሕክምና ዕውቀት እንዲጎለብትና የተሻለ የጤና ሥርዓት እንዲኖር ከማገዙም በላይ፣ በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ድንበር ተሻጋሪ የጤና ችግሮችን በጋራ ለመለየትና ለመቆጣጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግም ያነሳሉ።   ዛሬ በነጭ ጋውን፤ ትናንት በሰማያዊ ቆብ የዛሬውን ምስል ለመረዳት ወደ ትናንቱ መመለስ ያስፈልጋል። ዛሬ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ኮሪደሮች የሚታዩት ከደቡብ ሱዳንና ከሩዋንዳ የመጡ ወጣት ሐኪሞች ናቸው። ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት ግን በእነዚያ ሀገራት የሚታዩት በሰማያዊ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር መለያ ያሸበረቁ ኢትዮጵያውያን የሰላም አስከባሪዎች ነበሩ። ዛሬ ግን ቦታው ተለውጧል፤ ዩኒፎርሙ ተለውጧል። ነገር ግን ተልዕኮው አልተለወጠም። ያኔ ሰላምን በማረጋጋት ሕይወትን ከጦርነት መታደግ ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ሕይወትን ከበሽታ የመፈወስ ተልዕኮ ነው። በዚህ መልኩ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት ሚና ከአንድ መልክ ወደ ሌላ ቢሸጋገርም፣ መሠረታዊ ዓላማው ግን አልተቀየረም። ይህም ሰላምን መገንባት፣ ሰውን ማገልገልና ጎረቤቶችን ማጠናከር ሆኗል። የኢትዮጵያ የሰላም ማስከበር ታሪክ በ1950ዎቹ በኮሪያ በታዋቂው "ቃኘው ሻለቃ" የተጀመረ ሲሆን፣ በመቀጠል በኮንጎ፣ በላይቤሪያ፣ በቡሩንዲ፣ በሱዳን፣ በደቡብ ሱዳንና በሶማሊያ ድረስ የታሪክ ማህደር የተዘረጋ ነው። ይህም በታሪክ ድርሳናት መጻሕፍት ላይ የሚነበብ ብቻ አይደለም፤ ዛሬ በአዲስ አበባ በሚማሩ የአፍሪካ ወጣት ሐኪሞች ሕይወት ውስጥ በሕያው መልኩ ጎልቶ ይታያል። ሩዋንዳ፤ የኢትዮጵያ የማይረሳ ውለታ በ1994 ሩዋንዳ የተከሰተው የዘር ፍጅት በሰብዓዊነት ላይ የተቃጣ የአፍሪካና የዓለም ጥቁር ታሪክ ሆኖ ተመዝግቧል። በዚያ አስቸጋሪ ወቅት ብዙዎች ሩዋንዳን በሩቅ ሆነው ሲመለከቱ፣ ኢትዮጵያ ግን ከሰላም አስከባሪዎቿ ጋር በመቆም የሰው ልጅ ሕይወት ከማንኛውም ጉዳይ እንደሚቀድም በተግባር አሳይታለች።   ይህን ታሪክ የሚያስታውሱት በኢትዮጵያና በጅቡቲ የሩዋንዳ አምባሳደር ቻርለስ ካሮምባ ናቸው። እሳቸው እንደሚሉት፣ ''ሩዋንዳ በከባድ ፈተና ውስጥ በነበረችበት ወቅት ኢትዮጵያ ያደረገችልን ውለታ በሩዋንዳዊያን ልብ የታተመ፤ በሀገራቱ የግንኙነት ታሪክ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጭምር በወቅቱ የነበረው የኢትዮጵያ ወታደራዊ ልዑክ አባልና ተሳታፊ ነበሩ፤ ይህ በሀገራቱ መካከል ያለው ጥብቅ ቁርኝት ማሳያ ነው።'' ስለዚህ ዛሬ አንድ ሩዋንዳዊ ወጣት በአዲስ አበባ ተምሮ ወደ ሀገሩ ሲመለስ፣ ያ ጉዞ በድንገት የተጀመረ አይደለም፤ ከሦስት አስርት ዓመታት በፊት የተዘራ የመተማመን ፍሬ ዛሬ በዕውቀት እየጎመራ መሆኑን ነው። ሀገራ አቋራጭ ወንዝ እንደ ደም ሥር፤ ኃይል እንደ አዲሱ የትስስር ቋንቋ የሀገራት ጉርብትና በሰላም ማስከበርና ግጭት ማረጋገጥ በሚደረግ ትብብር ብቻ አይደለም፤ በሚጋሩት ዕውቀት፣ የተፈጥሮ ሀብትና በሚገነባ የጋራ ዕድገትም ጭምር ነው። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የቀጣናውን ግንኙነት ከፖለቲካ ግንኙነት መገለጫነት ወደ ተግባራዊ ትብብር ለመቀየር የቻለችባቸው መስኮች ብዙ ናቸው። የኤሌክትሪክ ኃይልና የውሃ ሀብት ትብብርም ወሳኞቹ የመተሳሰሪያ ማዕከሎች ናቸው። ዛሬ ከኢትዮጵያ የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል የጅቡቲን ኢንዱስትሪዎች ያንቀሳቅሳል፤ በኬንያ የከተሞችን መብራት ያበራል፤ ወደ ሱዳንና ታንዛኒያ በማቅናትም የቀጣና ትስስር መስመር እየዘረጋ ነው። ይህም የኢትዮጵያ ዕይታ የእርስ በርስ መተማመንን የሚገነባ የሰላም መሠረት ነው።   ውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ደኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ጥምረት ማዕቀፍ ውስጥ ቀጣናውን በኃይል የማስተሳሰር ታሪካዊ ሚናዋን ይበልጥ አጠናክራ ትቀጥላለች። የኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርም የጋራ ልማትን እያሳለጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አንድ ሀገር የጎረቤቷን ቤት የሚያበራ ኃይል ስታቀርብ፣ በተመሳሳይ ጊዜ የጋራ ዕጣ ፈንታንም እየገነባች መሆኑን ያመላክታል። ይህንን እውነታ የደቡብ ሱዳን የውሃና መስኖ ሚኒስትር ጀምስ ማዊች ሲገልጹት፤ ''ኢትዮጵያ የውሃና የኃይል ልማቷን የምታከናውነው ለራሷ ብቻ ሳይሆን የቀጣናውን የጋራ ተጠቃሚነት መርህ በማስቀደም ጭምር ነው።''   በተመሳሳይ አረንጓዴ አሻራን የመሳሰሉ የአካባቢ ጥበቃ ፕሮግራሞች ከአንድ ሀገር ድንበር አልፈው ለመላው ዓለምና ቀጣናዊ የአየር ንብረት ደኅንነት ጉልህ ፋይዳ ያበረክታሉ። ወንዞች በሀገራት ካርታ ላይ ድንበር አያውቁም፤ የአየር ንብረትም ፓስፖርት አይጠይቅም። ስለዚህ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ትብብር ትዕምርትና የጋራ ህልውና ጉዳይ ነው። የኢኮኖሚ ትስስር፤ የአዲሱ ዓለም የዕድገት ምኅዋር እንደ ዶክተር ኒክሰን ያሉ ወጣቶች የኢትዮጵያን ታሪክ በሆስፒታል ውስጥ እየኖሩ ሲሆን፣ የቀጣናው የወደፊት ታሪክ ደግሞ በንግድ፣ በመጓጓዣና በኢኮኖሚ ትስስር እየተገነባ ነው። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት በቅድሚያ ለጎረቤት መርህ የተቃኘ መሆኑ የሚታየው በዲፕሎማሲ መድረኮች ብቻ አይደለም። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ላይ የረጅም ዘመን የታሪክ ባለቤትና ከበርካታ ሀገራት ጋር የቆየ የንግድ ትስስር ያላት ሀገር ናት። ይህንን የንግድ ዲፕሎማሲዋን ይበልጥ ለማዘመንና ለማስፋፋት በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደ ብሪክስ (BRICS) ባሉ ጥምረቶች በንቃት በመሳተፍ ላይ ናት። የዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባል ለመሆንም የጀመረችውን የድርድርና የዝግጅት ጉዞ በቁርጠኝነት እያስቀጠለች ትገኛለች። በአህጉር ደረጃም ቀድሞ በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ የጋራ ገበያ (ኮሜሳ)፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና (AfCFTA) አማካኝነት ቀጣናዊና አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስሯን በማጠናከር የአፍሪካን የጋራ ገበያ ዕውን ለማድረግ እየተጋች ነው። ይህ አጠቃላይ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የንግድ ስትራቴጂ ነው። ለዚህ ማሳያም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቀን ሶስት ጊዜ ወደ ሩዋንዳ መዲና ኪጋሊ የሚያደርጋቸው የቀጥታ በረራዎች፣ የቀጣናውን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርና የንግድ ፍሰት እጅግ እያቀላጠፉት መሆኑ ነው። በአሁኑ ወቅት የሁለቱ ሀገራት የንግድ ሚዛን ተመጣጣኝ ደረጃ ላይ ነው። ሩዋንዳ ወደ ሰባት ሚሊዮን ዶላር ገደማ የሚጠጋ ምርት ከኢትዮጵያ ስታስገባ፣ በምላሹ ደግሞ ስድስት ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ምርቷን ወደ ኢትዮጵያ ትልካለች። ወደ 40 የሚጠጉ የኢትዮጵያውያን ኩባንያዎች በሩዋንዳ ውስጥ በንግድና ልማት ሥራዎች ተሰማርተዋል። እነዚህ ኩባንያዎች በአጠቃላይ ከ73 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ካፒታል ይዘው መንቀሳቀሳቸው፣ ትስስሩ ከቀላል የንግድ ግንኙነት አልፎ የሀገራቱ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ሕይወት ወደ ማስተሳሰር ደረጃ መሸጋገሩን የሚያሳይ መሆኑን አምባሳደር ቻርለስ ካሮምባ ይገልጻሉ። መደምደሚያ፡ የድንበር ልጅ... የአፍሪካ ተስፋ ትናንት የኢትዮጵያ ወታደሮችና የሰላም አስከባሪዎች የቀጣናውን ሀገራት ሰላም ለመጠበቅ ኪጋሊና ጁባ ዘምተዋል። ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያና በደቡብ ሱዳን ድንበር አካባቢ አንድ ሕፃን ልጅ ጎረቤቶች በፍቅር ሲኖሩ ይመለከት ነበር። ዛሬ ያ ሕፃን በአዲስ አበባ ሕይወት የሚያድን ዶክተር ሆኗል። ነገ ደግሞ ወደ ሀገሩ ተመልሶ የሚያክማቸው ሕፃናት የሚያገኙት ሕክምና፣ በኢትዮጵያ የተቀሰመ ዕውቀት ይሆናል። ምናልባት የዚህ ታሪክ ትልቁ ትምህርት ይሄ ይሆናል። ሀገራትን በጣም የሚያስተሳስራቸው ነገር ስምምነት ብቻ አይደለም፤ የአንዱ ሕዝብ ልጅ በሌላው ሕዝብ ልጅ ሕይወት ውስጥ የሚያሳርፈው አሻራ ነው። ዶክተር ኒክሰን፣ ዶክተር ሲስቶና ዶክተር ሙሂር የተማሩትም የሕክምና ትምህርት ብቻ አይደለም፤ ድንበርን በሰብዓዊነት መሻገር የሚቻልበትን የአፍሪካ አዲስ ትርክት እንጂ። ስለዚህ ይህ የአንድ ወጣት ሐኪም ጉዞ ብቻ አይደለም፤ ይህ ከድንበር መንደር የተጀመረ፣ በጥቁር አንበሳ ነጥሮ የወጣና በአፍሪካ የወደፊት ተስፋ የሚያስቀጥል የጋራ ታሪክ ነው። ይህ የታሪክ፣ የደም፣ የጥበብ፣ የውኃ፣ የኤሌክትሪክ ኃይልና የንግድ ትስስር የአፍሪካ ህብረት የሚያልማትን የበለጸገችና የተሳሰረች አፍሪካ በተግባር ለማየት እንደሚቻል የሚያመላክት ህያውና ተስፋ ሰጪ ምስክር ነው።
የኢትዮጵያ ማኛ ወርቅ፤ ከተንጣለለው የጎጃም ማሳ ወደ ዓለም ገበያ
Jul 14, 2026 946
በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞኑ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የጤፍ ምርት ከሚገኝባቸው አካባቢዎች መካከል ይጠቀሳል። ለዚህ ስኬት የተፈጥሮ ጸጋው ብቻ ሳይሆን የአርሶ አደሮች ትብብር፣ ዘመናዊ የእርሻ አሰራርና የገበያ ትስስር መጠናከር ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። የተንጣለለው የምስራቅ ጎጃም ማሳ በጤፍ ተሸፍኖ ማየት ስሜትን ይገዛል። በማሳው መካከል ደግሞ አርሶ አደሮች በጋራ እየሰሩ መመልከት ከትውልድ ትውልድ የተላለፈ የመረዳዳትና ለሺህ ዘመናት ለዘለቀ አስተራረስ አብነት ነው። የጎጃም ጤፍ በጥራቱ ቢታወቅም፣ ምርቱን በተሻለ ዋጋ ለመሸጥ የሚያስችል የገበያ ትስስር ውስን ነበር። አርሶ አደሩ በብዙ ድካም ያመረተውን ምርት ለደላሎች በዝቅተኛ ዋጋ ለመሸጥ ይገደዳል። በምርቱ ላይ የሚፈጠረው እሴትም እምብዛም ነው።   ዛሬ ግን ያ ታሪክ እየተለወጠ ይመስላል። በደብረ ማርቆስ ከተማ የተቋቋመውና የማኛ ጤፍ ዱቄትን ወደ ዓለም ገበያ መላክ የጀመረው ፋብሪካ የአርሶ አደሩን ምርት በቀጥታ በመቀበል ወደ እሴት የሚቀይር ድልድይ ሆኗል። ከእርሻ ወደ ፋብሪካ፣ ከፋብሪካ ወደ ውጭ ገበያ የሚዘልቀው ይህ የእሴት ሰንሰለት የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማሳደግ አዲስ የለውጥ ምዕራፍን ከፍቷል። የማኛ ጤፍ ዱቄት ማምረቻ ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ ሰማኸኝ ጌታቸው እንደሚገልጹት፣ ፋብሪካው በቀን በአማካይ ከ600 እስከ 800 ኩንታል ጤፍ የሚፈጭ ሲሆን፥ ሥራ በጀመረባቸው ጥቂት ወራት ውስጥ 600 ቶን እሴት የተጨመረበት ጤፍ ለውጭ ገበያ አቅርቧል። በዚህም አንድ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለሀገር አስገኝቷል። ይህ አሃዝ የጤፍ ምርት በፋብሪካ እሴት ሲጨምር የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ ጥቅም በግልጽ ያሳያል ብለዋል። ከዚህ በላይ ደግሞ ፋብሪካው ለ70 የሚጠጉ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩ የግብርና ልማት ከኢንዱስትሪ ጋር ሲሰናሰል የሚፈጠረውን ተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያመለክታል። ይህ ማለት አንድ የጤፍ ሰብል ከማሳ እስከ ውጭ ገበያ ድረስ በሚያደርገው ጉዞ በርካታ የሥራ ዕድሎችን፣ የገቢ ምንጮችንና የኢኮኖሚ እሴቶችን ይፈጥራል ማለት ነው። በምስራቅ ጎጃም ዞን ትርፍ አምራች ከሆኑ አካባቢዎች መካከል በደጀን ወረዳ የሚገኙ አርሶ አደሮችም ይህንን ለውጥ በቀጥታ እየተጠቀሙበት ነው። በክላስተር ማረስ የምርት ጥራትን በማሻሻል ጉልህ ጠቀሜታ ያስገኛል። ኢዜአ ከዚህ ቀደም በወረዳው በኩታ ገጠም የጤፍ ምርት ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን በጎበኘበት ወቅት የተመለከተው እውነትም ይህንኑ ነው። ፋብሪካው ደግሞ ከተጠቃሚነት ላይ ተደማሪ ጠቀሜታ የሚያገኙበትን ዕድል ፈጥሯል።   በደጀን ወረዳ በክላስተር ተደራጅተው ጤፍን በስፋትና በጥራት ከሚያመርቱ አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር መኩሪያው ታደለ አንዱ ሲሆኑ፤ የኩታ ገጠም እርሻ የጉልበት ወጪን በመቀነስ የምርት ጥራትና ብዛትን በማሳደግ ከፍተኛ ውጤት እንደሚያስገኝ ይገልፃሉ። በክላስተር ማምረት በአንድ ጊዜ መዝራት፣ መከታተልና መሰብሰብ በመቻሉ የምርት ብክነትን መቀነስ እንደተቻለም ሌላው አርሶ አደር ሸጋው ከፍያለው ያብራራሉ።   እንደ እርሳቸው ገለጻም፤ አርሶ አደሮች በአንድነት መስራታቸው የግብርና ሥራዎችን በወቅቱ ለማከናወን አስችሏል። ይህም በምርታማነት ላይ ቀጥተኛ አወንታዊ ተፅዕኖን ፈጥሯል። በተመሳሳይ አቶ ውዱ ሞሱ እንደሚሉት፤ የአርሶ አደሮች መተባበር ከዘር እስከ ምርት አሰባሰብ ድረስ በሁሉም ሂደት ውጤታማ አድርጓቸዋል። ምርቱ ሲደርስም በደቦ በመሆን በአጭር ጊዜ በመሰብሰብ የጊዜና የጉልበት ብክነትን አስቀርቷል።   የአርሶ አደሩ ስኬትም በማሳ ብቻ የሚቆም አይደለም። ከምርቱ መገኛ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው ደብረ ማርቆስ ከተማ የተቋቋመው የማኛ ጤፍ ዱቄት ማምረቻ ፋብሪካ ሥራ መጀመሩ የደጀንና የአካባቢውን አርሶ አደሮች ከማሳ በቀጥታ ወደ ዓለም ገበያ የሚያገናኝ አዲስ የእሴት ሰንሰለት ፈጥሯል። ከዚህ ቀደም ጤፍ እንደ ጥሬ ምርት ብቻ ይሸጥ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ ግን በፋብሪካ ተበጥሮ፣ ተፈጭቶ፣ በዘመናዊ መልክ ታሽጎ እሴት ተጨምሮ ወደ ውጭ ገበያ እየተላከ ነው። የደብረ ማርቆስ ከተማም በዚህ ሂደት የኢንዱስትሪ ማዕከል እየሆነች ነው። በከተማዋ የሚገኙ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የአካባቢውን ጥሬ እቃ በመጠቀም እሴት የሚጨምሩ በመሆናቸው ግብርናን ከኢንዱስትሪ ጋር የሚያስተሳስሩ የልማት ሞዴሎች እየሆኑ መጥተዋል። ይህም ለጎጃም ብቻ ሳይሆን ለመላው ኢትዮጵያ የግብርና ሽግግር አቅጣጫን የሚያሳይ ጠቃሚ ልምድ ነው። የኢትዮጵያ ጤፍ በባህላችን ያለውን ክብር ተጠብቆ በዓለም ገበያም ተፈላጊነቱን እያሳደገ ነው። ይህን ዕድል በተሻለ መንገድ ለመጠቀም የምርት ጥራትን ማሻሻል፣ የማቀነባበር አቅምን ማስፋት፣ የአርሶ አደሩን የገበያ ትስስር ማጠናከርና ተመሳሳይ የእሴት ጭማሪ ኢንዱስትሪዎችን በሌሎች አምራች አካባቢዎች ማስፋፋት ቀጣዩ የልማት ምዕራፍ ይሆናል። ከጎጃም የተንጣለለ የእርሻ ማሳ የሚነሳው የጤፍ እህል ዛሬ በፋብሪካ እሴት ተጨምሮ ወደ ዓለም ገበያ እየተጓዘ ነው፤ ይህም የኢትዮጵያ ግብርና ከባህላዊ አመራረት ወደ እሴት ጭማሪ ኢኮኖሚ እየተሸጋገረ መሆኑን የሚያሳይ ተጨባጭ ውጤት ሆኗል።   የደብረ ማርቆስ ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ተመስገን ተድላ፣ ከተማዋ ለኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ተመራጭ እየሆነች የመጣችው በቂ ጥሬ ዕቃ፣ የሰው ኃይል፣ የተሻለ የመጓጓዣ አገልግሎትና የሰላም ሁኔታ በመኖሩ መሆኑን ያብራራሉ። በተለይም የጎጃም አካባቢ የግብርና ሃብት ለእሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎች ጠንካራ መሠረት እየፈጠረ መሆኑን ይጠቅሳሉ። በለውጡ ዓመታት 253 የአምራች ኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ መግባታቸውና አብዛኞቹ ወደ ምርት መሸጋገራቸው የአካባቢው ኢኮኖሚ እያደገ መምጣቱን ያሳያል። ከእነዚህ መካከል የጤፍ ማቀነባበሪያ ፋብሪካው የጎጃም ማኛ ወርቅ የሆነውን የጤፍ ምርት እሴት ጨምሮ ወደ ዓለም ገበያ በማቅረብ ለአርሶ አደሩ፣ ለከተማዋና ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ተጨባጭ ጥቅም የሚያስገኝበትን አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል ይላሉ። በዚህ መልኩ በምስራቅ ጎጃም ዞን ያለውን ሰፊ የጤፍ ምርት በደብረ ማርቆሱ ፋብሪካ እሴት ተጨምሮ ወደ አውሮፓና አሜሪካ ገበያ መድረሱ የኢትዮጵያ ግብርና ከጥሬ ምርት ሽያጭ ወደ እሴት ጭማሪ፣ ከአካባቢ ገበያ ወደ ዓለም ገበያ እየተሸጋገረ መሆኑን በግልጽ ያሳያል። ይህም ጤፍ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የሚያጠናክር ስትራቴጂያዊ ሀብት መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን አብራርተዋል።  
ለብሩህ ነገዋ በአዲስ ምዕራፍ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ
Jul 14, 2026 688
ለብሩህ ነገዋ በአዲስ ምዕራፍ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ በሙሴ መለሰ ረጅም ታሪክ፣ቱባ ባህልና ሕብረ-ብሔራዊነት መለያዋ የሆኑት ኢትዮጵያ፣ የነገ ተስፋዋን አስተማማኝ ለማድረግ አዲስ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል ይበልጥ ብሩህ ለማድረግ ሀገራዊ ምክክር ቁልፍና ታሪካዊ ሚና ይጫወታል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በመላ ሀገሪቱ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ አጀንዳዎችን የመሰብሰብ ስራ ያጠናቀቀ ሲሆን ነገ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በይፋ ይጀመራል። ኮሚሽኑ በመላ ሀገሪቱ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡትን ሀሳቦችን በማደራጀት ለዋናው ሀገራዊ ምክክር የሚቀርቡ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን በይፋ ለይቷል። እነዚህም የሀገር ግንባታ ታሪካዊ ሂደቶች፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች የአዲስ አበባ እና የድሬደዋ ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታ፣ የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር፣ እንዲሁም የሰላም ግንባታ ናቸው። ስምንቱን መሠረታዊ አጀንዳዎች መነሻ በማድረግ የሚደረገው ውይይት፣ የፖለቲካ መረጋጋትን ከመፍጠር ባለፈ ለአስተማማኝ የኢኮኖሚ እድገትና ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። ምክክሩ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ያለው ፋይዳ እጅግ የጎላ ነው።ባለፉት የታሪክ ሂደቶች የተፈጠሩ ቅሬታዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በሰላማዊ ውይይት በመፍታት፣እርስ በርስ ለመደማመጥ እና ታሪካዊ ቁስሎችን በይቅርታ ለመፈወስ የሚያስችል ዋነኛ መንገድ ነው። ከጠመንጃና ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሀሳብ የበላይነት የሚነግስበትን፣አለመግባባቶችና ልዩነቶች በሰላማዊ ውይይትና በንግግር የሚፈቱበትን ባህል ያሰፍናል።ይህም ልዩነቶችን በመቀበል በአንድነትና በጋራ መኖር የሚያስችሉ የጋራ እሴቶችና ሀገራዊ መግባባቶች ለማጠናከር ይረዳል። ከዚህም ባለፈ፣ምክክሩ ለተቋማዊ እድገትና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዋነኛ ምሰሶ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ መልካም አጋጣሚን ይፈጥራል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ የሚጀመረውን ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አስመልክቶ ዛሬ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ምክክሩ ፍቱን የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን፣ የእኛን እና የመጪውን ትውልድ እጣ ፈንታና የወደፊት ተስፋ ሙሉ በሙሉ የሚወስን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ጭምር ነው ሲሉ ገልጸውታል። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፣ዛሬ ሀገራችን የምትሻው ጠመንጃ ያነገቡ ሳይሆን በሀሳብ ብስለት፣ በእውነት፣ በዕውቀትና በጽናት ታጥቀው የተሰናዱ የሰላም ታጋዮችን ነው ያሉ ሲሆን እኛ ዛሬም እንደ ትናንቱ በታላቅ የድል ዋዜማ ላይ እንገኛለን፤ ምክንያቱም የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ ማሸነፍ አይቀሬ ነው ብለዋል። ይህንን በጎ ዕድል ለመጠቀምም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንነትና በኃላፊነት ስሜት በመሳተፍ ለሀገር ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ሀገራዊ ምክክር የኢትዮጵያን መጻኢ ዕድል በራስ አቅምና ጥበብ ለመወሰን የሚያስችል ትልቅ እድል ነው።የኢትዮጵያ መጻኢ ተስፋና ሁለንተናዊ ብልጽግና ከሀገራዊ ምክክሩ ስኬት ጋር የተሳሰረ ነው። ባለፉት የታሪክ ሂደቶች ውስጥ የተፈጠሩ ቅሬታዎችን በንግግር መፍታት፣ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሃሳብ የበላይነት የሚነግስበትን ምቹ መደላድል ይፈጥራል። ዛሬ በምክክሩ ጠረጴዛ ዙሪያ የሚታየው የመነጋገር እና የመደማመጥ ባህል እንዲሁም ችግሮችን በውይይት ብቻ የመፍታት አማራጭ የተሻለች ኢትዮጵያን እውን የሚያደርግ ታሪካዊ መሰረት ይጥላል።
ትንታኔዎች
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ
Jul 3, 2026 4279
ምክክር-ለኢትዮጵያ ብሩህ ነገ (በቀደሰ ተክሌ ከኢዜአ-ሚዛን አማን ቅርንጫፍ) ጥቃቅን ችግሮች እያደጉ ሔደው ሀገር የማፍረስ አደጋን ከመደቀናቸው በፊት ከሥር መሠረቱ ማስተካከያ ማድረግ ብቸኛው መንገድ ሁሉን አካታች ሀገራዊ ምክክርን ማካሔድ ነው። በዚህም ራሳቸውን ከመጥፋት ታድገው ሀገር በሚል ስያሜ ሕልውናቸውን ያቆዩ ሀገራት አሉ። ከእነዚህም መካከል በአካታች ምክክር ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተሸጋገሩትን ማንሳት ይቻላል። ለአብነት የቱኒዚያ ሀገራዊ ምክክር በዓለም ላይ ካሉ የቅርብ ጊዜ ስኬታማ ተሞክሮዎች ቀዳሚው ነው። እ.አ.አ በ2011 የ"አረብ አብዮት" መነሻ የነበረችው ቱኒዚያ፣ የፖለቲካ መሪዎች መገዳደል እና ከፍተኛ አለመረጋጋት ገጥሟት ነበር። አራት የሲቪክ ማህበራት (የሰራተኞች ማህበር፣ የጠበቆች ማህበር፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የነጋዴዎች ማህበር) በጋራ በመሆን "የቱኒዚያ ብሔራዊ ምክክር ኳርትት አቋቋሙ። ፖለቲከኞችን አስገድደው በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲቀመጡ አደረጉ። በዚህም ሳቢያ ሀገሪቱ አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ህገ-መንግስት ቀረጸች፤ ሰላማዊ ምርጫ ተካሄደ፤ ሀገሪቱ ወደ ለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት ከመግባት ዳነች። ይህንን ምክክር የመሩት አራት ድርጅቶችም እ.አ.አ በ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አግኝተዋል። ደቡብ አፍሪካም ለዘመናት የዘለቀውን የዘረኝነት እና የአፓርታይድ ስርዓት ያቆመችው በጦርነት ሳይሆን በሁሉን አካታች ብሔራዊ ምክክር ነው። በኔልሰን ማንዴላ የሚመራው ኤ.ኤን.ሲ እና የነጮች ገዥ ፓርቲ በጥላቻ ፋንታ "ለነገዋ ሀገር" በሚል ይቅርታን እና ድርድርን አስቀደሙ። በምክክሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና የነገዶች ተወካዮች በሙሉ ተሳትፈዋል። ያለምንም ደም መፋሰስ የስልጣን ሽግግር ተደረገ፤ በአለም ላይ እጅግ ተራማጅ የሚባል አዲስ ህገ-መንግስት ተቀረጸ፤ "የእውነትና የእርቅ ኮሚሽን" በማቋቋም ያለፈው ቁስል እንዲሻር ተደረገ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሁዋን ማኑኤል ሳንቶስን የኖቤል ተሸላሚነት ያበቃው ምክክር የተካሄደው በኮሎምቢያ መንግስት እና በኤፍ.ኤ.አር.ሲ አማፂያን መካከል ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀው እና ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ላለቁበት ጦርነት እልባትን ሰጥቷል። ምክክሩ ከሀገር ውጭ (በኩባ እና ኖርዌይ) በተደረጉ ድርድሮች የተደገፈ ሲሆን፣ ዋናው ትኩረቱ ግን የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ እና የአደንዛዥ ዕፅ ንግድን ማቆም ላይ ያተኮረ ነበር አማፂያኑ ሙሉ በሙሉ ጦርነቱን አቁመው ነፍጣቸውን አስረክበው፤ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲነት በመቀየር ሰላማዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ያስቻለ ነው። ኢትዮጵያም ዛሬ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣን ዕዳ በጫንቃዋ ላይ ተሸክማ ቆማ ያንን አሳራፊ መድኃኒት ሽታለች። በዘመነኛው ዓለም ውስጥ ሆና በትላንት በሽታ ትታመማለች። የቀደሙት የጣሉት የስህተት እርሾ ዛሬም ከሊጥ ጋር እየተቦካ የኮመጠጠ የአኗኗር ሥርዓትን ትውልዱ እንዲጋፈጥ ምክንያት መሆን ከጀመረ ከራርሟል። ይህም የማይነጋ ሌሊት መስሎ ታይቶ ብዙዎችን ለቀቢጸ-ተስፋ ዳርጓል። የሰላም በር ዘግቶ ሰላም መፈለግ፣ መክፈቻ ቁልፍ በእጅ ይዞ ወደ ሌላ ማማተር ሆነና ነገሩ፤ ችግሩ ከነግሳንግሱ እያደገ ጥቁር ደመናን በሀገሬ ሰማይ ላይ ለመጋረድ አቅሙን ተጠቀመ። ሆኖም እንደተባለው የማይነጋ ሌሊት፣ የማይፈታ ሕልም የለም። "ፈጣሪም ሀገርን ያለ አንዳች አይተውም" ነውና ቃሉ፤ የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ፈነጠቀ። ወደ ውስጥ የሚመለከት፣ የራስ ማንነትን በኢትዮጵያዊ ቀለም የሚፈትሽ፣ ችግርን ሳይሆን መፍትሔን አነፍንፎ ገሃድ የሚያወጣ፣ ሀገር በቀል ዕውቀትን ያከበረና መልካም የሆኑ ነባር እሴቶችን ለችግሮቻችን ወጌሻ ያደረገ የለውጥ ተስፋ ከተፍ አለ። የመጋቢት ብስራት ኢትዮጵያን ወደ ፍካት ለመለወጥ በሀገር ፍቅር ስሜት አዳዲስ የሰላም መንገዶችን መክፈት ጀምሯል። ከመገፋፋት ይልቅ መደመርን፣ ከመካሰስም ይቅርታን የሚያስቀድመው የመደመር መንግሥት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ ሀሳብ ይዞ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋሙ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስብል ተግባር በኢትዮጵያ ተወጠነ። በፖለቲካ እሳቤም ሆነ በሐሰት ትርክት አልያም የማያግባባ የትኛውንም ጉዳይ በመምዘዝ አኩርፎ ነፍጥ ማንገብን ልምድ ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት ባለበት፤ በአንጻሩ አቅም ኖሮት ሥልጣን የጨበጠ በሀሳብ የተቃረነውን በሚኮንንበትና ቀፍድዶ በወህኒ ቤት በሚያሰቃይባት ምድር በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መመካከር ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ በደማቅ የታሪክ ቀለም የሚመዘገብ ክስተትም ነው። ምክክር በባህላችን አብሮን የኖረ የማንነታችን አካል የሆነ እሴታችን ቢሆንም ለፖለቲካው ሜዳ ግን እንግዳ ነገር ነውና። ጠላቶቻችን የኢትዮጵያን ሰላምና ዕድገት ማየት አይሹምና ሂደቱን ለማደናቀፍ ጥረዋል። በዚህም የመለወጥ መንገዳችንን ለመዝጋት ብዙ ጉድጓዶችን ምሰዋል። ጉድጓድ ለማዘጋጀት ከሩቅ ያመጡት ቁሳቁስ የለም፤ ከራሳችን ጋር አብሮ ባደገው የዘርኝነት፣ የጽንፈኝነትና አክራሪነት ገሶ (ትልቅ የጉድጓድ መቆፈሪያ) ነው እንጂ። በተለይ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝኃ-ብሔር እና ሃይማኖት ብዙ ሳይደክሙ ያጠመዷቸው ፈጣን ውጤት የሚያስገኙላቸው ወጥመዶች ነበሩ። የወል ትርክት በሐሰተኛ ትረካ ተሞልቶ ለብዙዎች ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሆነ። ጠንካራዋ ሀገር ኢትዮጵያ ግን መሠረቶቿ ዓለት ላይ ስለሆኑ ይህ ሁሉ የጥፋት ጎርፍና ነፋስ ሊያነቃንቃት አልቻለም። ይልቁንም በጽናት ቆማ ወጀብ ማዕበሉን ጸጥ የሚያደርግ ሀገርኛ መሣሪያ ታጥቃለች - የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን! በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ አማረ ፈንታው (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን መቋቋምና በአግባቡ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አጠናቆ አጀንዳ መለየት መቻሉ የኢትዮጵያውያንን የሥነ-ልቦና እና የሞራል ከፍታ ማሳያ ነው። ለዚህም አመክንዮ ሲያስቀምጡ፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለችግር መፍቻ ወደ ጠረጴዛ ሳይሆን ወደ ጫካ የሚሮጥ የፖለቲካ ሥርዓትን ነው ስታስተናግድ የቆየችው ብለዋል። ዛሬ ላይ ግን ያ ልክ አለመሆኑን የተረዳ ትውልድ በስብዕና ሞራል ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖን አሳድሮ በጥይት ሳይሆን በሀሳብ ለማሸነፍ ራሱን አዘጋጅቷል። በጦር ግንባር ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍትሔ ሊያገኝ ከራሱ ጋር ተስማምቷል። ይህ የመማርና የማደግ ውጤት ነው። የትናንት አካሔድ ሞትና ችግርን እንጂ ብልጽግናን አላተረፈም። መመካከር በእጃችን የነበረ አውጥተን ያልተጠቀምንበት ሀብታችን ነው። እንደ ተፈጥሮው ሁሉ እሴታችን የተሸፈነበት አቧራ በምክክር ተራግፎ በአብሮነት እና ዘላቂ ሰላም የምንደምቅባትን ጀንበር ልናይ ንጋት ላይ ተቃርበናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ትልቅ ተስፋ የጣለበት ጉዳይና ውጤቱን አጥብቆ የሻተበት አጀንዳ ምን ይሆን ተብሎ ቢጠና፤ "የምክክር ኮሚሽን ወደ ተግባር መግባት" ከሚለው በላይ ሌላ አጀንዳ ይኖራል ብሎ በልበ-ሙሉነት መግለጽ አይቻልም። ያለ ልዩነት ሁሉም ደግፎ በብርቱ ናፈቀው። የጥንት የአያት ቅድመ-አያቱ ወግ ነባርና አዲስ ሳይሆንበት በብርሃን ፍጥነት ዓላማውን ተረዳ። ተረድቶም ሳይቀር ተስፋውን ወደ ሚጨበጥ ውጤት ለመቀየር ባለው አቅም ሁሉ ለመደገፍ ተረባረበ። ዕድል የገጠመውም በቁርጠኝነት ሂደቱ ላይ ተሳተፈ። የዚህ ድምር ውጤት የምክክር ኮሚሽኑ ለኢትዮጵያ የነበሩ አለመግባባቶች ቁልፍ መፍቻዎች ናቸው ያላቸውን 8 ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎችን በስኬት ለመለየት አበቃው። የምክክሩ አጀንዳ ልየታ ሥርዓት ከአጀንዳ መለየት ያለፈ ትርጉም ያለው ነው። ስኬታማ የተቋም ግንባታ አንጸባራቂ ክስተት ጭምር እንጂ። አካታችነትን ባረጋገጠ መልኩ የሁሉንም አካባቢ ወግ፣ ባህልና ሥርዓት ተገንዝቦ ለሀገር የሚሆን አጀንዳ በስኬት መሰብሰብ የተቋማዊ ብቃት ማሳያ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ማድረግ የምትችል መሆኗን ገላጭ ሌላኛው የድል ገጽ ቢባል ግነት አይሆንም። አጀንዳዎቹ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች መፍታት የሚያስችሉ ናቸው። ኃይል የተሞላበት የፖለቲካ ሥርዓትን በመገርሰስ ወደ ዴሞክራሲያዊ እና የተሟላ የሰላም ደሴት የሚያሸጋግር አጋጣሚ እንደሚሆንም ዶ/ር አማረ ይገልጻሉ። ምክክሩ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ሲሆን በታሪክ ድርሳን የምናስቀምጠውና ወደፊት መጪው ትውልድ የሚያወሳው ኩነት ነው ብለዋል። መምህር ቢመርቅ በርሁን በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር ናቸው። እርሳቸው የምክክር ኮሚሽንን ተግባር ለኢትዮጵያ ያለውን መልካም ዕድልነት ሲገልጡ፤ ስር የሰደዱ ችግሮችን ከሥር የሚነቅል መሣሪያ ብለውታል። ከግለሰቦች የፖለቲካ ትርክት ተላቆ ወደ ተቋማዊ አሠራር መሸጋገሪያ ድልድይም እንደሆነ እንዲሁ። ኢትዮጵያ በበርካታ ነጠላ ትርክቶች ለሰላም እጦት ተዳርጋለች፣ በግለሰቦች ግላዊ ፍላጎት ብዙዎች ሕይወታቸውን ገብረዋል። ይህ የመጠፋፋት ሰንሰለት ይበጠስ ዘንድ ምክክሩ አስፈላጊ ነው። ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተግባራት ስኬት አካታችነት ትልቅ አቅም እንደሆነውም መምህር ቢመርቅ ያነሳሉ። በኮሚሽኑ የተሠራው የአጀንዳ ማሰባሰብና ልየታ እንዲሁም የምክክሩ ተሳታፊ መረጣ ሂደት በተማሩ ኃይሎች አልያም በፖለቲካ ልሂቃን ላይ ብቻ መሠረት ያደረገ አይደለም። በታችኛውም እርከን ወርዶ አርሶ አደሩን፣ አካል ጉዳተኛውንና ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችን የጉዳዩ ባለቤቶች ናችሁ ብሎ ማሳተፉ በጎ ውጤት አመልካች ቅድመ-ሂደት ነበር ነው ያሉት። የአካታችነቱ ወሰን መስፋት ሰፊውን የማኅበረሰብ ጥያቄ ይዞ ለመነሳት አስችሎታል። የሁሉም ጥያቄ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ማለትም፦ በሀገር ግንባታ፣ በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ እንዲሁም በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልና እና በምርጫ ሥርዓት፣ በፌዴራል ከተሞች (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደር) ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሕግ የበላይነት እና በሰብዓዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ሥር ተጠልሏል። እነዚህ አጀንዳዎች በአንድም በሌላም የመከፋፈል፣ በጎሪጥ የመተያየትና የጥርጣሬ መንፈስን በመንዛት ዜጎች እርስ በእርስ ከመተማመንና በአብሮነት ከመቀጠል ይልቅ "የኔ" የሚል አጥር ውስጥ እንዲገቡ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል "ተበደልኩ"ን ወልደው ኩርፊያን አስፍተዋል። ይህም በአንድ ወገን ሳይሆን ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በተለያየ መጠን የሚንጸባረቅ ችግር ነው። አሁን የመጣ ሳይሆን ትናንት የነበረ፣ ለዛሬ የተዘራና እንክርዳድ እያበቀለ ያለ የግጭት ዘር ነው። ሀገራዊ የሆኑ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የአስተዳደር ሥርዓት ፈትሾ እውነትን እና ለነገ የሚበጀውን የወል ትርክት በሕዝብ ይሁንታ ሊያጸና ቀጠሮ የያዘው ኮሚሽኑ፤ በሁሉም ዜጎች ትብብር ሀገራዊ ድልን ያጎናጽፋል። ሰላምና ስኬት ለኢትዮጵያችን! አበቃሁ!!  
በመደመር የተቃኘ ኢትዮጵያን የሚመጥን የከተሜነት ጉዞ
Jul 3, 2026 3376
በዮሐንስ ደርበው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ዓላማ ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኚ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። ትናንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሣሠር የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ! የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫወት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁን እንጂ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል። ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚሁ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዓለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዓለም አቀፍ፣ አኅጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት በውጤታማነት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ መሰረተ-ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ኮሪደር ልማት ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል።
ትላንትን ከዛሬና ከነገ ጋር ማስተሳሰር - የመደመር መንግስት እይታ በቱሪዝም
Jul 1, 2026 3349
በዮሐንስ ደርበው ቱሪዝም ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመላው ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ በአህጉራችን አፍሪካም ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙበት ሃገራት እንዳሉ ይታወቃል። ቱሪዝም ከገቢነት ከኢኮኖሚያዊ እቅምነት ባለፈ ትውልድን ያስተሳስራል ብሄራዊ ትርክትን ለመገንባትም ያግዛል ። ትላንትን ከዛሬ ዛሬንም ከነገ ጋር የሚያስተሳስር ነው። “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግስት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ በማድረግም ይጠበቅባቸዋል።
ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!
Jun 24, 2026 7138
በዮሐንስ ደርበው በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆኑት ሁሉ ማለት ነው። ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው። የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ጀምሮ ይካሄዳል - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ትውልዱ ዛሬንም ነገንም በሚጠቅመው የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ ንቁ ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል የአረንጓዴ ዐሻራ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋት ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በአንጻሩ በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል? በምክክር ሁሉንም አሸናፊ አድርጎ መቋጨት እየተቻለ ለበርካታ ዓመታት የሐሳብ ልዩነቶች የወለዷቸው ግጭቶች፤ እንደ ሀገር አያሌ ሰብዓዊ፣ ቁሳዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ እና ማኅበራዊ ክስረቶች ማስከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል። የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው። ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት። ይህም ፍላጎትን በኃይል ለመተግበር ሕይወትና ንብረት ከሚያወድመው ጦርነት ይልቅ አዋጭ የመግባቢያ መንገድ መሆኑን ያሳያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል። እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር በአካታችና አሳታፊ ውይይት ወደ የጋራ መግባባት መድረሻ አትራፊ መንገድ ነው። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ኃላፊነቱን ለመወጣት ለምክክር በሩን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ክፍት አድርጓል። በዚህም መሠረት ከዳያስፖራው፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በተለያዩ ክልሎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩና ሰላምን ከመረጡ ብሎም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ፤ አጀንዳዎችንም ተቀብሏል። ኮሚሽኑ የመጨሻው የምክክር ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የሚገልጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ አካታች የምክክር ጉባዔ ለማካሄድ በማንኛውም ጊዜ ወደ ምክክሩ ለሚመጡ አካላት በሩ ክፍት መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኪንታሮት ህመም እንዴት ይከሰታል? እንዳይከሰት መከላከል የሚቻልበት ብልኀትስ አለ? 👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል? የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል። 👉 ሀገሬው ለበለጸገችና ጠንካራ ሀገሩ ምን ይጠበቅበታል? መንግሥት በኢትዮጵያ የሐሳብ ገበያን ባሕል ለማድረግ እየተከተላቸው ካሉ መንገዶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በመደመር መንግሥት መጽሐፍ (ገጽ 383) ላይ እንደሰፈረው ደግሞ፤ በኢትዮጵያ የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፤ በምክክርና ውይይት ጎልብተው አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ስለሀገር የሚያገባው ሁሉም አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ሐሳብ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር መሆኑም ተገልጿል። ስለዚህ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚከናወነው ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ኢትዮጵያውያን ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተመረጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ጉባዔ ማካሄድ የሚችሉበትን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ሀገራዊ ምክክር በአንድ በኩል፤ አንድነትና ኅብረትን በማጠናከር ልሂቃንና ሕዝብ ለአንድ ከፍ ላለ ዓላማ በአንድ ላይ እንዲቆሙ ያደርጋል። በዚህም ጥረቶች ሁሉ በአንድ አቅጣጫ እንዲፈስሱ ያደርጋል። በሌላ በኩል ፖለቲካዊ መረጋጋትና ሰላምን በመፍጠር የመንግሥት ትኩረት፣ ሀብትና ጊዜ ሳይበታተን ብልጽግናን ለማረጋገጥ ብቻ እንዲውል ያደርጋል (የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 403)። #እንመካከር! #በምክክር_ከሰፈር_እስከ_ሀገር_የተሻለ_ነገን_እንገንባ! #ኢዜአ #Ethiopian_News_Agency #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው  
ልዩ ዘገባዎች
በታዳጊው የተሰራችው መኪና 
Jun 17, 2026 10429
ለአዳዲስ ፈጠራ የማይታክተው ልጅዓለም ንጉሱ ትውልድና እድገቱ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ ፀመራ ቀበሌ ነው። ከሕጻንነቱ ጀምሮ ፈትቶ መግጠምና አፍርሶ መስራትን እየተለማመደ የመጣው ልጅዓለም፤ ከቤት እስከ ትምህርት ቤት ያልተቋረጠ ፈጠራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህ ቀደም ለሚማርበት ፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከወዳደቁ ቁሶች የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችን በመስራት የፈጠራ አሻራውን አኑሯል። በትምህርትና በፈጠራ ሥራው ገፍቶበት አሁን ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ልጅዓለም እንጨት ገጣጥሞ መኪና በመስራት ያለውን የጥበብና ፈጠራ ክህሎት አሳይቷል። በታዳጊው የተሰራችውና በፔዳል የምትነዳው መኪና ሁለት ሰዎችን የማያዝ አቅም አላት። በቀጣይ ተጨማሪ ቁሶችን በማቅረብና በተለያየ መንገድ የሚያግዘው ካገኘ መኪናዋ በዲናሞ እንድትንቀሳቀስ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።   የተሽከርካሪውን አካል የገጣጠመው በአካባቢው አጠራር "እንቋ" የተሰኘ ዛፍ እንጨትን በመጠቀም ሲሆን የተሽከርካሪውን እግር ለማዘጋጀት ደግሞ የዋርካ ዛፍ ተጠቅሟል። በዚህም መሰረት የልጅዓለም መኪና የመብራትና የመሪ ስራዋ ተጠናቆ ሁለት ሰዎችን ጭና መንቀሳቀስ እንደምትችል በተግባር አሳይቷል። "በቀጣይ የሚያግዘኝና የሚደግፈኝ ካገኘሁ በዲናሞ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለመስራት ዝግጁ ነኝ" ያለው ጥበበኛው ተማሪ ወደ ፊት ለሀገሬ ብዙ የመፍጠር ህልም አለኝ ብሏል። የፀመራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ ጌቴ፤ ከዚህ በፊት ተማሪ ልጅዓለም በትምህርት ቤቱ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዳሉት አስታውሰው ትምህርቱንም ፈጠራውንም አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።   የፈጠራ ክህሎቱን፣ ተሰጥኦውንና ፍላጎቱን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ ተከታትያለሁ ያሉት መምህሩ የሳይንስ ትምህርቱንና የግል ክህሎቱን ደምሮ ለአዳዲስ ሥራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተው፣ የመኪና ፈጠራውም ይህንኑ በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል። የግብዓት አቅርቦት ድጋፍ ከተደረገለት የተሻለና ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚችል ገልጸው ለሚፈጥሩ ወጣቶች በጥሩ ምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጨት የተገጣጠመችው መኪና በሁላችንም ድጋፍ የዲናሞ፣ የብረትና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች ከተሟሉላት በታዳጊው ጥበብ የተሻለች መኪና ሆና ልትሰራ ትችላለች ሲለም እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 20681
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 13725
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 19477
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 101767
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 76906
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 56064
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 53613
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 38613
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 38222
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 37709
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 36647
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 101767
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 76906
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 56064
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 53613
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ቱሪዝም- የኢትዮጵያ የማከናወን ዐቅም ማሳያ
Jun 29, 2026 6716
በዮሐንስ ደርበው “ሀገራችን ከቱሪዝም ልታገኛቸው የምትችላቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አካባቢያዊ ጥቅሞች ሁሉ ከቀረው ዓለም ጋር ተወዳድራ እንድታገኝ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጎብኚ ወደ ሀገራችን መሳብ አለብን። ለዚህም የተለያዩ ስልታዊ መላዎች ነድፈን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን (የመደመር መንግሥት 273)። የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የለውጡ መንግሥት እመርታዎችን ካስመዘገበባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። መንግሥት ከአምሥቱ የትኩረት መስኮች አንዱ አንድርጎም በጥናት፣ አካባቢያዊ ፀጋን ዐውቆና ለይቶ በተደመረ ዐቅም ባከናወናቸው ሥራዎች በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ፣ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ እና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት እሠየው ያሰኙ ተግባራት አከናውኗል። የብርቱዎቹ ልጆች ብርታት በቀጣይ ...! በገበታ ለሸገር የተገለጠው የተደመረ ዐቅም - ለኢትዮጵያ ስኬቶች እንደማሳያ የመልከ መልካሟ ብዙ መልኮች ለአስም በሽታ አጋላጭ ምክንያቶችና ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው ከእንጦጦ - ቀበና የተከናወነው የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትም ለጎብኚም ለነዋሪም ምቹ ከባቢን በመፍጠር ረገድ እየተደረገ ያለውን ትጋት ያስረዳል። ምረቃውን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ፤ “መቆሸሽ እኛ አይገባንም፣ መጠልሸት እኛ አይገባንም፣ ማነስ እኛ አይገባንም! ሠርተን እንደምንችል ማሳየት ያስፈልጋል” ሲል የሥራውን ማራኪነትና ውበት ገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚሁ ወቅት፤ ‎የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ሲሉ በቀጣይ ካለፈው የበለጠ እንደሚሠራ አመላክተዋል። ገንዘብን፣ ዕውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሐሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል ሲሉም አስገንዝበዋል። በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው (ገጽ 256) ላይም፤ “የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ሀገራት በዘመናቸው ሁሉ የሠሩትንና ተፈጥሮ ያደለቻቸውን መልካም ገጽታ በኩራት ለዓለም የሚያስተዋውቁበት፣ ‘ሀገሬ ይሄንን ትመስላለች’ የሚሉበት መድረክ ነው። ሀገርን በሚያኮራና ለሌሎች ለመጋበዝ በማያሳፍር መልኩ መገንባት፣ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሠረቱ ነው።” ያሉትም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በቁጭት መነሳታቸውን ይገልጻል። ነገን ዛሬ እየሠራች ያለችው ኢትዮጵያ ካላት ላይ ሳትነፍግ የገንዘብም ሆነ የሰው ኃብቷን ቱሪዝም ላይ ስታውል፤ አንድም የኢንዱስትሪውን ዐዋጭነት ብሎም የዜጎቿን በየዘርፉ ዘላቂ ተጠቃሚነት በመገንዘብ ነው። እዚህ ላይ ለሀገር ገቢ በማስገኘት እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ዘርፉ የሚያበረክተውን ጥቅም ማጤን ይገባል። በአዲስ አበባ ከተከናወኑ ቁልፍ የቱሪዝም ልማቶች መከካከል፤ የመስቀል ዐደባባይ ቅርስን ማንበርና ማዘመን፣ ከአዲስ አበባ ልማት ጋር ተሣሥሮ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ መልክ የታደሠው ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት፣ የአምሥቱ ዕውቀት ተኮር ማዕከላት (አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የሀገር በቀል ዕጽዋት ማሳያ፣ የአንድነት ቤተ-መዛግብት እና የማዕድን ሙዝየም) ግንባታ፣ የአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል እና ሌሎችም ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ጎብኚዎች የሚያርፉበት ሎጂና ሆቴሎች ግንባታም በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። ገበታ ለሸገር ብሎ ከአዲስ አበባ የተነሳው የቱሪዝም ልማት በገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ወደ ክልሎች ተስፋፍቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ሎጂዎች እንዲገነቡ አስችሏል። የተገነቡት ሎጂዎች ደግሞ ለጎብኚዎቹ ምቾትን የሚያስጠብቁ መሠረተ-ልማቶችን ስበዋል። በርካታ ጎብኚ መሳብና ገቢን ማሳደግ፣ በጎ ገጽታን መሸጥ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የበለጸገች ኢትዮጵያ ዕውን ማድረግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት ሁሉ ግቦች ናቸው። መንግሥት ዕምቅ የጎብኚዎች መስኅብ ዐቅም የሆኑና አቧራ ለብሰው የተደበቁትን ፀጋዎች ውበታቸውን ገላልጦ እያሳዬ ያለውም ለዚህ ነው። ቱሪዝም በቀጥታ ዜጎች (ሰዎች) የሚጠቀሙበት ኢንዱስትሪ ነው። ለዚህ ደግሞ ሰዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና መጠበቅ ይኖርባቸዋል።መሠረተ-ልማቶችን በመጠበቅ እንዲሁም ከመንግሥት ጎን በመሆን በሚፈለጉበት ሁሉ ንቁ ተሳትፎ ማድረግም ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ጠቅላላ ምርጫ ምክክር - ወደ መግባባት መሻጋገሪያው ድልድይ! ያልተቋረጠ የስኬት ጉዞ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ቱሪዝም #PMOEthiopia #በኢዜአ_ዐይን #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ
Jun 26, 2026 4599
ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት - የሕዝብ ድምጽ ኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ፍኖቷ ለአፍሪካ አርአያ ሆና አሳይታለች... የአፍሪካውያን ቀንዲል ናት። የክፉ ቀን መሸሸጊያቸው፣ የመከራ ጊዜ መጽናኛቸው፣ የነጻነት ተምሳሌትና የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በረጅም ዘመናት ታሪካዊ መስተጋብር የተፈጠረ የሀገረ መንግሥት መዋቅር ባለቤት ናት። በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ ምድሯን ሰንጥቀው በሚያልፉ ወንዞቿ የምትታወቅ አገር ናት። የተለያዩ ማዕድናት በብዛት የሚገኙባት ከመሆኗም በላይ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህልና እሴቶች ሕብር ሠርተው፣ ተስማምተው የሚኖሩባት የታሪክ ማህደር ናት። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ግርማ ሞገስና የነጻነት አርማነት፣ በውስጣዊ የፖለቲካ ጉዞዋ ውስጥ ካጋጠሟት መዋቅራዊ ስብራቶችና የሥልጣን ፍትጊያዎች ሊታደጋት አልቻለም። ለዘመናት በሀገሪቷ የሰፈነው የሥልጣን ሥርዓት የሰፊውን ሕዝብ ፍላጎትና ተሳትፎ ያገለለ፣ በጥቂት የሕብረተሰብ ክፍሎችና ልሂቃን ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረተ ነበር። ይህ አካሄድ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ አንዱን ሥርዓት በሌላው እየተካ፣ የተተካው አገዛዝ ደግሞ የባሰ ጭቆናን ይዞ የሚመጣበትን አዙሪት ፈጥሯል። ከብዙ መቶ ዓመታት የዘውድ አገዛዝ በኋላ የመጣው ወታደራዊ ሥርዓት፣ በመቀጠልም ለ30 ዓመታት ገደማ የዘለቀው የአንድ ወገን የበላይነት የሰፈነበት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሀገሪቱንና ዜጎቿን ለከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ዳርገው አልፈዋል። ይህ ዓይነቱ የመከራና የጭቆና ሰንሰለት ግን በ2010 ዓ.ም በተቀጣጠለው ሀገራዊ ለውጥ ተገርስሶ ወደ አዲስ የፖለቲካና የዴሞክራሲ ምሕዳር ተሸጋግሯል። ያለፉትን ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ጉዞ ስንመረምር፣ ሀገሪቷ ከአሮጌውና ከተለመደው የአፈና ሥርዓት ወጥታ አዲስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኛ አቅም ይዛለች። ይህ ወቅት የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ መብት በተግባር የተረጋገጠበትና የሐሳብ ብዝኃነት የተስተናገደበት ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም የሥልጣን ማራዘሚያ ሆነው ያገለግሉ የነበሩ ዋና ዋና ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው እንዲደራጁ መደረጉ የለውጡ ትልቁ ስኬት ሆኖ ሊጠቀስ ይችላል። በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ የለውጡ የመጀመሪያ ፍሬ የታየው በ2013 ዓ.ም የተካሄደው ስድስተኛው ምርጫ ነበር። በወቅቱ የነበሩትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተቆቁሞ ሕዝቡ ያሳየው የባለቤትነት ስሜት የዴሞክራሲ ናፍቆቱን በግልጽ ያሳየ ነው። ይህንን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጥ የነቃ አስደናቂ የፖለቲካ ተሳትፎ አሳይቷል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ታሪካዊ መድረክ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን የማይናወጥ አቋም አሳይተውበታል። ከንጋት እስከ እኩለ ሌሊት ረጅም ሰዓታትን ተሰልፈው የተፈጥሮ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችንና ልዩ ልዩ ፈተናዎችን በሙሉ በትዕግሥት በመሻገር ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ይህ ሂደት የሚያሳየው ሕዝቡ የሥልጣን ምንጭነቱን በተግባር የተረዳበትና ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የወሰነበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ነው። በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ጉዞና የውስጥ መረጋጋት ሁልጊዜም በከፍተኛ ትኩረት የሚከታተሉት ጉዳይ ነው። ላለፉት ዓመታት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሚነሱ ሥጋቶችና የጂኦፖለቲካ ጫናዎች ቢኖሩም፣ ይህ በስኬት የተጠናቀቀው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቷን የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊነት በተግባር ያስመሰከረ ሆኗል። በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነፃነትና በሰላም ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት፣ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ በራሷ ዜጎች ፍላጎት የመወሰን ሙሉ አቅም እንዳላት ለዓለም አሳይቷል። ምርጫው ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያ ያሸነፈችበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን በመስጠት የሀገሩን ሉዓላዊነትና አንድነት አስከብሯል። የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም በሁከት ሳይሆን በሕዝብ የላቀ ውሳኔ ብቻ መሆኑን በማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካለፈችባቸው የፖለቲካ ስብራቶች በላይ ከፍ ብላ እንድትቆም አድርጓታል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተደማጭነትና የድርድር አቅም ከፍ የሚያደርግ ነው። የምርጫው ዝርዝር ስኬቶች ምን ምን ናቸው የሚለውን ስንመለከት፦ 👉የአፈሙዝ ድምፅንና የጽንፈኛ ዛቻን ያሸነፈው የሕዝብ ጽናት ግንቦት 24 ታሪካዊ ቀን ናት። በዚህች ታሪካዊ ዕለት፣ በየምርጫ ጣቢያው በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሰጠው ሕዝብ ያሳየው የነጻነት፣ የሉዓላዊነት እና የጽናት ማረጋገጫ ነው። ምርጫውን ለማደናቀፍና ሕዝቡን ለማስፈራራት የተቃጡ የአፈሙዞች ድምፆችና የሁከት ዛቻዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ሕዝብ ከመምረጥ አላፈገፈገም። መራጮች የጽንፈኛ ኃይሎችን ዛቻ ወደ ጎን ትተው፣ የአካላቸውን ሕመም፣ የበሽታን ሥቃይ፣ አልፎ ተርፎም የወሊድ ምጥንና የቅርብ ዘመድ ሞት ያመጣውን ጥልቅ ሐዘን በሕሊናቸውና በሥጋቸው ተሸክመው ነበር ረጅሙን ሰልፍ ተሰልፈው ይበጀኛል ያሉትን በካርዳቸው የመረጡት። ይህ የሚያሳየው እውነት ለኢትዮጵያውያን የምርጫ ካርድ ሰላማቸውን የሚገዙበት፣ መብታቸውን የሚያስከብሩበትና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በገዛ እጃቸው የሚወስኑበት ብቸኛ የነጻነት አዋጃቸው መሆኑን ነው። ሕዝቡ ከምርጫ ውጭ በሆነ መንገድ፣ በኃይል ወይም በሁከት ሥልጣን ለመያዝ ምኞትና የቆየ የሥልጣን ናፍቆት ላላቸው ወገኖች በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግልጽና የማያሻማ መልዕክት አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኃይልና የሁከት አካሄድን እንደማይቀበል፣ በድምፅ ላይ ብቻ የተመሠረተ ሕጋዊ ሥርዓትን ለማፅናት እንደሚታገል አረጋግጧል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በአፅንኦት ሲያነሱ፤ "የዘመናችን ዲሞክራሲ አስተምህሮቱ ሰላምና ዕድገት፣ ቋንቋው ደግሞ መምረጥና መመረጥ ብቻ በመሆኑ የፖለቲካ ቅኝታችሁንና አካሄዳችሁን ከዚሁ ስልጡን መስመር ጋር ማስተካከል ይበጃችኋል። ካሁን በኋላ የሕዝብ ድምፅ ያልጎበኘው፣ የምርጫ ካርድ ያልዳሰሰው የፖለቲካ ሥልጣን መያዣ መንገድ በኢትዮጵያ ዝግ መሆኑን እነሆ እንዳየነው መሠረት የጣለ ስለሆነ ይህኑ ስልጡን መንገድ ለመቀበል የማትፈቅዱ ሁሉ ግን ግፋ ቢል የዘመናችን የፖለቲካ ድርሳን ሲጻፍ ልትሆኑ የምትችሉት የግርጌ ማስታወሻ ብቻ ነው።" ብለዋል። ስለሆነም ከዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕጋዊ አካሄድ ውጭ የሚደረግ ሙከራ የጥፋት ተዋናይ ከመሆን ባሻገር ለሀገር የሚያተርፈው አንዳች ነገር እንደሌለ በዚህ ስሑት መንገድ ላይ የሚገኙ አካላት ሊገነዘቡ ይገባል። 1. ምርጫው በቁጥሮች ሲገለጽ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጉልህ የሚጠቀሱ አኃዛዊ መረጃዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ እንደገለጹት፤ ቦርዱ ከ120 ሚሊዮን በላይ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ ሀገር አሳትሞ ካስመጣ በኋላ፣ ከምርጫው 4 ቀናት በፊት በሀገሪቱ ባሉት ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በታማኝነትና በጥንቃቄ ማድረስ ተችሏል። ይህንን እጅግ ግዙፍና ውስብስብ የሎጂስቲክስ ሥራ ሙሉ በሙሉ ያከናወኑት የቦርዱ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች ብቻ መሆናቸው ተቋማዊ አቅሙ ምን ያህል እንደጎለበተ ማሳያ ነው። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ እንደተናገሩት፤ የቦርዱ ሠራተኞችና የምርጫ አስፈጻሚዎች በዕረፍት ቀናትና በሌሊት በመጋዘን ውስጥ ጭምር እያደሩ የቁሳቁስ ማሸግ ሥራዎችን በትጋት አከናውነዋል። ሩቅና ተደራሽነታቸው አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ ቁሳቁሶችን በእግር፣ በእንስሳት ጀርባና በጀልባ ጭምር በማጓጓዝ፣ ወንዞችን ለመሻገር የራሳቸውን የፕላስቲክ ጀልባ ሠርተው ሀገራዊ አደራቸውን ተወጥተዋል። በድምፅ መስጫ ቀን ሥራቸውን ከንጋት እስከ ንጋት በልዩ ብርታት ፈጽመዋል። ይህ ልብ የሚነካ እውነታ የሚያሳየው፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታና የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር የሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ዋጋ ያለው የተናጥልና የጋራ ትጋት የሚጠይቅ መሆኑን ነው። ሰፊ ተሳትፎ፦ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 80 የግል ዕጩዎች ተሳትፈዋል። 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲና የግል ዕጩዎች ተወዳድረዋል። ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓርቲዎች ፖሊሲዎቻቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህ ተግባር ፓርቲዎች ከምርጫው ውጭም ራሳቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ባህል ያዳብራል። የመራጮችና አስፈጻሚዎች ቁጥር፦ በአጠቃላይ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፤ ምርጫውን ለማስፈጸም ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። ታዛቢዎችና ወኪሎች፦ ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያሰማሯቸው ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች፣ እንዲሁም 63 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ ታዛቢዎች ተሳትፈዋል። ለመራጩ ሕዝብ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት መስፈርቱን ላሟሉ 169 ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጥቷል። እንዲሁም 21 ሚሲዮኖችና አንድ የውጭ ሀገር የምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ምርጫውን ተመልክተዋል። የአየር ሰዓት አጠቃቀም፦ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ነፃ የአየር ሰዓት የማግኘት መብት ስለነበራቸው ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 752.5 ነፃ የሬዲዮ ሰዓት፣ 57.5 ነፃ የቴሌቪዥን ሰዓትና 576 የጋዜጣ ኮለምን በዘመናዊ የዕጣ ማውጣት ሥርዓት ተደልድሎ እንዲጠቀሙ ተደርጓል። መገናኛ ብዙኃን፦ 73 የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃንን የወከሉ 1 ሺህ 827 የሀገር ውስጥና 45 የውጭ ጋዜጠኞች ለዘገባ ሥራ ተሰማርተዋል። የሕግ ማሻሻያ እና ዲጂታላይዜሽን፦ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ተሻሽሎ በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 ተተክቷል። ቦርዱ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር፦ ለመጀመሪያ ጊዜ በገለልተኛ ባለሙያዎች የሚመራ፣ እያንዳንዳቸው 2 ሰዓት የሚወስዱ 19 የክርክር መድረኮች በቦርዱ ተዘጋጅተዋል። 14ቱ በአማርኛ፣ 5ቱ በክልል ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ሲዳምኛ፣ አፋርኛ) ተካሂደው በሰባት መገናኛ ብዙኃን በፕራይም ታይም ተላልፈዋል። አካታችነት፦ 28 ሺህ 632 የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ከ20 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲመዘገቡ ተደርጓል። የቅሬታ አፈታትና ክትትል፦ የቅድመ አደጋ ማሳወቂያ ሥርዓት (Early Warning System) ተዘርግቷል። 663 የምርጫ ክልል ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎችና ልዩ የአጣሪ ጉባኤ ተደራጅተው 129 አቤቱታዎችን መርምረዋል። የሕግ ጥሰት በተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት እንዲኖር ተወስኗል። 2. ጠንካራና ገለልተኛ ተቋም፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሀገር ውስጥ አቅም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠነ ሰፊ ተቋማዊና ሕጋዊ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ከመሆኑም በላይ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ ሀገራዊ አቅምን በተግባር ያሳየ ነበር። የዚህ ምርጫ ትልቁ ትርፍ ጠንካራና የማይናወጡ ብሔራዊ ተቋማትን መገንባት መቻላችን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያሳየው ፍጹም ገለልተኝነት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ብቃት እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የመተግበር አቅም፣ ተቋማት ከግለሰቦችና ከፖለቲካ ጫና በላይ መሆናቸውን ያስመሰከረ ነው። ይህም ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አስተማማኝ የመንግሥት መዋቅር መሠረት ነው። ለምርጫው ስኬት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መራጮችን በትዕግሥት በማስተናገድ፣ ብቁ አስፈጻሚዎችን በማሰማራትና ሂደቱን በታማኝነት በመምራት ረገድ ቦርዱ አድናቆት የተቸረው ሥራን ፈጽሟል። የሠራተኞቹ ቀንና ሌሊት መትጋት እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት አመራር አባላት ያሳዩት ቁርጠኝነት የላቀና ለሀገር ኩራት የሆነ ተግባር ነው። በዚህ ምርጫ ውስጥ ትልቁን ትኩረት የሳበውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት ነው። ይህ ዘመናዊ አሠራር ለምርጫው ከተመዘገቡ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች መካከል ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በአካል መጓዝ ሳይጠበቅባቸው፣ ባሉበት ቦታ ሆነው በነፃነት እንዲመዘገቡ ዕድል ፈጥሯል። ቴክኖሎጂው የመራጮችን ማንነት በፎቶግራፍ ጭምር በማረጋገጡ በድምፅ መስጫ ቀን ሊፈጠሩ የሚችሉ ግድፈቶችንና ማጭበርበሮችን በከፍተኛ ደረጃ መከላከል ተችሏል። የዚህ ሥርዓት ዋነኛውና ትልቁ ድል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለጸገ መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የዚህን የቴክኖሎጂ ስኬት አስፈላጊነት ሲያብራሩ፤ "እነዚህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓቶች በውጭ ሀገር አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች የለሙ ሳይሆን በራሳችን ወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተገነቡ ናቸው። ይህም ተቋሙን ከውጭ አቅራቢዎች ጥገኝነት ነፃ በማድረግ በራሱ አቅም እንዲቆምና ለወደፊቱ ማሻሻያዎችን በራሱ እንዲያከናውን መሠረት ጥሏል።" ይህ እርምጃ ቦርዱ የውጭ የቴክኒክ ጥገኝነትን በመቀነስ የሀገር ውስጥ አቅምን ለመገንባትና የሉዓላዊነትና የደኅንነት ዋስትናን በራስ ቴክኖሎጂ ለማረጋገጥ የቻለበትን ስትራቴጂካዊ አካሄድ በግልጽ ያሳያል። በተጨማሪም በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በውጭ ዜጎች ይሠራ የነበረው የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መተካቱ የተሳካ የእውቀት ሽግግር መኖሩን አሳይቷል። 3. ሕጋዊ ማሻሻያዎች፣ አካታችነትና ተጠያቂነት ዴሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው ዜጎች፣ በተለይም ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ያለ ፍርሃትና ጫና፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በፖለቲካዊ ሂደቶች እኩል መሳተፍ ሲችሉ ነው። ይህንን እውን ለማድረግ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በታዛቢነት በመሳተፍ፣ ሴቶች የዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዲጠቀሙና በሂደቱ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል። ቦርዱ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ ጾታዊ ጥቃትና ትንኮሳን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። ከዚህም በላይ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግብረ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ አቋቁሟል። በተጨማሪም የምርጫውን ግልጽነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ቀድሞ የነበረው አዋጅ ቁጥር 1162/2011 በአዋጅ ቁጥር 1394/2017 እንዲተካ የተደረገ ሲሆን፣ ቦርዱ ይህንን መነሻ በማድረግ 10 አዳዲስ መመሪያዎችን አጽድቋል። በነዚህ ማሻሻያዎች ውስጥ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደ ዋና መርህ የተወሰደ ነው። 4. ፈተናዎችን መጋፈጥና ገለልተኝነትን ማስከበር ይህ ሁሉ ስኬት ግን ያለ ፈተና አልመጣም። ምርጫው በተያዘለት ጊዜ አይካሄድም የሚሉ ጥርጣሬዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ተቋሙን ፈትነውት ነበር። ሆኖም ቦርዱ ጫናዎችን በመቋቋም ሕግና መርህን ብቻ ተከትሎ በመሥራት ምርጫውን ለስኬት ማብቃቱን ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያረጋግጣሉ። ቦርዱ በምርጫው ወቅት የተቋሙን ነፃነት ከማንኛውም ዓይነት ጫናና ጣልቃገብነት በመጠበቅ በሕግና በመርህ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል። በምርጫ አፈጻጸም የአሠራር ግድፈቶች እና ከፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ ቅሬታዎችን በመመርመር በአንዳንድ የምርጫ ክልሎች በድምፅ መስጫው ቀን ጭምር አስፈጻሚዎችን አሰናብቷል፤ በምርጫ ውጤቶች ላይም ውሳኔ ሰጥቷል። ይህም ቦርዱ ለሕግ የበላይነትና ለምርጫ ታማኝነት ያለውን ጽኑ አቋም ያሳያል። የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአንድ ተቋም ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች በፀሐይና በዝናብ ሳይበገሩ በትዕግሥት የሰጡት ድምፅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች (እንደ አፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ) እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው። 5. የምርጫው ግልጽነትና ዓለም አቀፍ እውቅና የምርጫውን ታሪካዊ ሂደትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት በሰፊው ተሳትፈዋል። ሂደቱን ለመዘገብ 73 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1 ሺህ 827 ጋዜጠኞች የዘገባ ሥራቸውን አከናውነዋል። ከ260 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች እና ከ64 ሺህ በላይ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ተሳትፈዋል። በተለይም በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጣቸው 55 የሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 60 ሺህ 277 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን የተከታተሉ ሲሆን፤ 169 ድርጅቶች ደግሞ ለመራጮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል። በአህጉር ደረጃም የኬንያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ60 በላይ ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና 26 የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ታዛቢዎች ሂደቱን በታዛቢነት ተከታትለዋል። ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ግልጽ፣ አሳታፊና ተዓማኒ ሆኖ በስኬት መካሄዱንም አረጋግጠዋል። 👉የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች ምስክርነት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሰጡት መግለጫ፣ የምርጫው ዕለት ሰላማዊ፣ ሥነ ሥርዓት የሰፈነበት እና ግልፅነት የታየበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት። በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ መተግበሩ ወጣቶችን መሳቡን፣ ዜጎች በትዕግሥት ሰልፍ በመያዝ ጥልቅ ፍላጎታቸውን ማሳየታቸውን፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅቱ የተሟላ መሆኑንና የምርጫ ሰዓት መራዘሙ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በመስተንግዶ ረገድም ወንበሮችና የምግብ አቅርቦቶች መኖራቸው ረጅሙን ሰልፍ ታጋሽ እንዳደረገውና ለአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱን አረጋግጠዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት "ቅኝ ግዛትን በአንድነት የተከላከለች Couch፣ ለአፍሪካ ነፃነት የቆመች እና የአህጉሪቱ ዋና ከተማ በሆነች ሀገር ውስጥ የተደረገው ይህ ምርጫ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ሊኮሩ ይገባል፤ ወደፊት ለመራመድም በሕዝቦች መካከል ያለውን የፖለቲካ እና የማኅበረሰብ ውይይት ይበልጥ ማሳደግ፣ ወደ ኋላ የተተዉ የሚሰማቸውን አካላት ወደ መድረኩ በማምጣት እና አካታችና የተባበረች ኢትዮጵያን መገንባት ያስፈልጋል" ብለዋል። በሌላ በኩል፣ የኡጋንዳ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ (IGAD) የምርጫ ታዛቢ ቡድን በሰባት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 28 ጣቢያዎችን በመጎብኘት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አውጥቷል። ቡድኑ ጣቢያዎቹ በሰዓታቸው መከፈታቸውን፣ በቂ ቁሳቁስና አስፈጻሚዎች እንደነበሩ፣ የሳጥኖች አስተሻሸግ የድምፅ ምስጢራዊነትን ያረጋገጠ መሆኑንና የድምፅ አሰጣጡ ያለምንም መሰናክል በጥሩ ሁኔታ መካሄዱን በመታዘብ ምስክርነቱን ሰጥቷል። ለአረጋውያን፣ ሕፃናት ለያዙ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ መሰጠቱንና መራጮች የሚቀመጡባቸው ወንበሮች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በማዘጋጀትና በመምራት ረገድ ከፍተኛ አስተዳደራዊና ኦፕሬሽናል አቅም ማሳየቱን አጉልቷል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ለሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ የተደረገውን የጋራ ቁርጠኝነት ያደነቀ ሲሆን፣ "ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ በተለይም የምርጫ አስተዳደርን ለማሻሻል፣ አካታችነትን እና ተዓማኒነትን ለማሳደግ የተነደፉ ዋና ዋና ቴክኖሎጂያዊ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተስተዋሉበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ሲል ቡድኑ ምስክርነታቸውን በአፅንኦት የገለጹት። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ "ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጠናከርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል እንዲመዘገብ አብረን ለመሥራት ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት እናረጋግጣለን።" ሲሉ ነው የተደመጡት። 6. የምርጫው ውጤት፣ የሕዝቡ ጽናትና የአሸናፊው ፓርቲ ከባድ ሸክም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል። በሌላ በኩል ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎችም በምክር ቤቶቹ ወንበሮችን ማግኘት የቻሉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) 13፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ስድስት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ሦስት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሦስት፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ሦስት፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሁለት ወንበሮችን አሸንፈዋል። በሌላ በኩል ኦብነግ፣ ጉህዴን፣ አርጎባ አንድነት ጀበርቲ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ፣ ኅብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፣ የጌዴዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው አንድ ወንበር ሲያገኙ 8 የግል ተወዳዳሪዎችም ምክር ቤት ለመግባት አሸንፈዋል። ይህን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ከሌሎች ጊዜያት ለየት የሚያደርገው ታላቅ ክስተት፣ መራጩ ሕዝብ በታጋሽነት ተሰልፎ የመምረጥ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ወደር የለሽ ጽናት ነው። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ይህንን የሕብረተሰብ አደራ "አሸናፊው ፓርቲ ትልቅ ሀገራዊ ሸክም የተጣለበት መሆኑን ብልፅግና ፓርቲ በሚገባ ይረዳል። ፓርቲያችን በማኒፌስቷችንና በአጠቃላይ በምርጫ ቅስቀሳችን ወቅት ለሕዝብ ቃል የገባናቸውን በተግባር ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይንቀሳቀሳል" ብለዋል፡፡ 👉የፉክክርና የትብብር ሚዛን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምሕዳር በቀጣይነት ሊመራበት የሚገባው ስልጡን መስመር በፉክክርና በትብብር መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቆ መጓዝ ነው። ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና በሀገር ግንባታ ላይ ሚና ካላቸው አካላት ጋር በብሔራዊ ጥቅም ላይ በትብብር ለመሥራት ያለው አቋም የጸና መሆኑን የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በሰጡት አስተያየት፤ "ባለፉት ዓመታት የጀመርነውን በፉክክርና በትብብር መካከል ሚዛን ጠብቆ የሚሄድ ጥረታችንን በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በምንሠራቸው ሥራዎች ሁሉ ሕዝቡን በማሳተፍ፣ በየጊዜው የሕዝቡን ግብረ መልስ በመስማት፣ ያንን እንደ ግብዓት ተጠቅመን የእቅድ አካል አድርገን ወደ ተግባር ለመተርጎም በቁርጠኝነት እንንቀሳቀሳለን።" ብለዋል። ይህ ዕይታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሕዝብን ድምፅና ግብረ መልስ በየጊዜው የሚያዳምጥ፣ እንዲሁም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ለሀገር ጥቅም በጋራ የመሥራትን ስልጡንና አካታች የአሠራር ሥርዓት መከተል መጀመሩን ያሳያል። 7. ዴሞክራሲና ምርጫው የሚገለጽባቸው አራቱ ምሰሶዎች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማለት አማራጭ የሌለው የህልውና ጉዳይና የሁለንተናዊ ብልጽግናችን መሠረት ነው። ብዝኃነትን በአግባቡ ማስተናገድ፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና ጠንካራ ሀገር መገንባት የሚቻለው በዴሞክራሲያዊ ምሰሶዎች ላይ በመመሥረት ብቻ ነው። መንግሥት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሲቪል ማኅበራት ሚና የማይተካና አዎንታዊ ሚና አላቸው። መራጩን ሕዝብ ከማስተማር፣ ሕገ መንግሥታዊ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም ከማስቻል፣ እስከ ሰላም እሴት ግንባታና በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የዜጎችን ባለቤትነት ከማረጋገጥ አኳያ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለጹት፣ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። አንደኛው ምሰሶ፦ ምርጫ የሰላም ዋስትና መሆኑን መረዳት ነው። ሕዝቡ ልዩነቶችን በፀብና በአምባጓሮ ከመፍታት አዙሪት ተላቆ፣ በሰላማዊ መንገድ የመሻገር ባህልን መርጧል። በነቂስ ድምፁን መስጠቱ ኋላ ቀር የአመፃ መንገድን ለሚከተሉ ሁሉ "በቃችሁ" የሚል መልዕክት ያስተላለፈበት ሲሆን፣ የሰፊው ሕዝብ ማዕበላዊ ድምፅ ከአሮጌው የብጥብጥ ባህል መላቀቅ እንደሚፈልግ ማረጋገጫ ነው። ሁለተኛው ምሰሶ፦ የምርጫ ውግንና ከሕዝብ ጋር መሆኑን ማወቅ ነው። የምርጫ ተዓማኒነትና ክብሩ የሚገለጠው ሥልጣን ከሚመነጭበት ከሰፊው ሕዝብ ሉዓላዊ መብትና ፍላጎት ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ነው። ምርጫ ከሚሰጠው ኃላፊነት በላይ ለእያንዳንዱ ዜጋ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻልና ከሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ጋር የተቆራኘ መሆኑን ሕዝቡ በትክክል ተገንዝቧል። ሦስተኛው ምሰሶ፦ የምርጫው የፖሊሲ ሐሳቦችና አማራጮች ከፍታ የታየበት ነው። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የክርክር መድረኮች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያነሷቸውን የፖሊሲ አማራጮች ሕዝቡ በጥንቃቄ አዳምጧል። እነዚህ ሐሳቦች ለሀገር ዕድገት፣ ለጠንካራ መንግሥትና ለሰከነ የፖለቲካ ባህል ግንባታ መሠረት እንዲሆኑ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕሊና ማስረፅ፣ በሰነድ በማዘጋጀትም መተግበር ይገባል። አራተኛው ምሰሶ፦ ምርጫ እንደ ማኅበራዊ ሀብት፤ ምርጫ ፖለቲካዊ ኩነት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማኅበራዊ ሀብት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የዚህን ማኅበራዊ እሴት አንድምታ ሲያብራሩም "ሕዝባችን ስለ ኢትዮጵያዊ ቀናነቱና ፍቅሩ ጩኸቱን ሳይሆን የምርጫ ካርድ ድምፁን፣ ስላቅና ሃኬትን ሳይሆን ትሑትነቱን፣ የትኛውንም የፖለቲካ ሐሳብ ቢያራምድ እንኳን ማኅበራዊና ሀገራዊ ፍቅሩን ከጎኑ ላለው ወገኑ አለመንፈጉን ያየንበት እጅግ የተዋበ መድረክ ነበር። ስለዚህ የኢትዮጵያ ምርጫ ከፖለቲካዊ ፋይዳው ባልተናነሰ ሁኔታ ማኅበራዊ ፋይዳውም ከፍ ያለ ትልቅ የማኅበራዊ መሠረትን የሰጠው ነው።" ብለዋል። 8. የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ሚና፦ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስብራቶች የመፈወስ ዕድል ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትና የፖለቲካ ሥርዓት ጉዞዋ ውስጥ በርካታ አኩሪ ታሪኮችን ብታስመዘግብም፣ በሂደቱ ውስጥ የተፈጠሩና ዛሬም ድረስ ሀገራዊ አንድነቷን፣ ሰላሟንና የዴሞክራሲ ግንባታዋን እየተፈታተኑ ያሉ ሥር የሰደዱ የፖለቲካ ስብራቶች መኖራቸው አይካድም። እነዚህን ለዘመናት የዘለቁ ስብራቶች በመጠገን ረገድ ይህ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሀገሪቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሻግር የሚችል ታሪካዊና ስትራቴጂካዊ ዕድል ይዞ መጥቷል። ምርጫው በበሰለና አካታች መንገድ በመመራቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ላይ ጉልህና አዎንታዊ አሻራ ማሳረፍ የሚችልባቸው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አሉት። እነዚህም፦ የቅቡልነት ስብራትን ማከም፦ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመንግሥታት ሥልጣን አመጣጥ አብዛኛውን ጊዜ ከኃይል ፖለቲካ ወይም ሙሉ በሙሉ ነፃ ካልሆኑ ምርጫዎች ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕዝባዊ ቅቡልነት ማጣት ለግጭቶች መነሻ ሲሆን ቆይቷል። ይህ ምርጫ ነፃና ታማኝ ሆኖ መካሄዱ አሸናፊው አካል ከሕዝብ የሚሰጠው እውነተኛ የሥልጣን አደራ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ይህም በገዥው አካልና በሕዝቡ መካከል ያለውን መተማመን በማደስ ረገድ ትልቅ ዕድል ይሰጣል። የሰላማዊ ሥልጣን ሽግግር ባህልን መገንባት፦ ሥልጣንን በአፈሙዝ የመያዝ ልምድ ሀገሪቱን በተደጋጋሚ ለድቀት የዳረጋት መሆኑ ብዙ ትምህርት ሰጥቷል። በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ወገኖች የሕዝብን ድምፅ አክብረው የሚቀበሉበት ድባብ መፈጠሩ ምርጫን ብቸኛ የሥልጣን መያዣና መልቀቂያ መንገድ የማድረግ አዲስና ጤናማ የፖለቲካ ባህል በሀገሪቷ ውስጥ እንዲለመድ ያደርጋል። በተቋማት ላይ ያለውን አመኔታ ማደስ፦ ሕዝቡ እንደ ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማት ባሉ ገለልተኛ መሆን በሚገባቸው ተቋማት ላይ ያለው እምነት መሸርሸሩ ሌላው ስብራት ሲሆን፣ ይህንንም ምርጫ በስኬትና በገለልተኝነት ማካሄድ መቻሉ የተቋማቱን ነፃነትና ብቃት በተግባር የሚያሳይ በመሆኑ ዜጎች በሀገሪቷ የሕግ የበላይነት ላይ ያላቸው እምነት መልሶ እንዲያገግም ያደርጋል። ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር፦ አካታች የሆነ ምርጫ ማካሄድ መሣሪያ ያነሱ ወይም በሰላማዊ መንገድ የሚያምፁ የፖለቲካ ኃይሎች ቅሬታቸውን በሕዝብ ድምፅ እንዲፈትሹ በር ይከፍታል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቶች ለመፈወስ የራሱ አሻራ ሊያኖር የሚችለው ሂደቱ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በርካታ የፖለቲካ ኃይሎችን ያሳተፈ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በንቃት የተሳተፈበት በመሆኑ ነው። በዚህም ምርጫው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ በራሱ ወደ ሰፊው ብሔራዊ ምክክር ለመሻገር እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ ያገለግላል። ማጠቃለያ፦ ምርጫው ለአፍሪካ ዴሞክራሲ የብርሃን ፍኖት አፍሪካ በፖለቲካዊ አለመረጋጋቶች፣ በወታደራዊ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ኢ-ሕገመንግሥታዊ መንገድ መምራት፣ የመንግሥት ግልበጣዎች እየተፈተነች ባለችበት በዚህ የታሪክ ምዕራፍ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ስልጡን መንገድ ምርጫዋን ማጠናቀቋ ለአህጉሪቱ አዲስ ፍኖተ ዴሞክራሲ ሆና እንድትወጣ አድርጓታል። 'የአፍሪካ ችግሮች የአፍሪካውያን መፍትሔዎች' የሚለውን መርህ በተግባር በማሳየት፣ የራሳችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በራሳችን አቅም መቅረጽ እንደምንችል ለዓለም አሳይተናል። በዚህ አስቸጋሪ አህጉራዊ ድባብ ውስጥ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ማዕከልና የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊና ፍትሐዊ መንገድ በስኬት ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለጫናዎች ሳትበገር፣ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ መድረክ ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል። የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላምና ደኅንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ፤ አህጉሪቱ ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ዲሞክራሲ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ሰላምና ልማት ሊመጡ የሚችሉት በጠመንጃ ኃይል ሳይሆን ሕዝብ በነፃነት የራሱን መሪ በሚመርጥበት ስልጡን መንገድ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሚሽነሩ አክለውም፦ "አህጉራችን ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ ምርጫ የላትም። ወደፊት ለመራመድ፣ ዕድገትን ለማረጋገጥና በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ከሁሉ የተሻለው መንገድ ዴሞክራሲ ብቻ ነው" ሲሉ በአፅንኦት ጠቅሰዋል። በአጠቃላይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ኢትዮጵያ ተቋማዊ አቅሟንና ሕጋዊ መሠረቷን በማጠናከር ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የተሻገረችበት እና የጋራ የትብብር አቅምን ያሳየችበት አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል። ለዚህም ስኬት በየሚናቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የጸጥታ ኃይሎች፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢ ቡድኖች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም ሀገር በቀል ታዛቢ ድርጅቶች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። በምርጫው ወቅት የተሰጠው የሕዝብ አመኔታና ድምፅ ለተመራጮች ትልቅ አደራና ኃላፊነትን ጥሏል። ያሸነፉ ፓርቲዎችና ዕጩዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለሕዝብ ፍላጎት ቅርብ የሆነ አገልግሎት በመስጠት፣ በታማኝነት፣ በቅንነትና ንጹሕ በሆነ ሕሊና በመሥራት የሕዝቡን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር ግዴታ አለባቸው። የምርጫው ትልቁና የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በተመራጮችና በሕዝብ መካከል በሚገነባው መተማመን፣ በሚረጋገጠው ዘላቂ ሰላምና ለሁሉም ተጠቃሚነትን በሚያሰፍነው ሀገራዊ ዕድገትና ብልጽግና ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም