ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ይገኛል
Jun 9, 2026 1256
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ ከሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ክልሎች መካከል የ816 ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። ከዚህም መካከል የ24 የምርጫ ክልሎች ውጤቶች በቦርዱ ተረጋግጠው መጽደቃቸውም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በሰጡት መግለጫ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደው ልዩ ምርጫ መጠናቀቁንም ገልጸዋል። ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1ሺህ 139 ምርጫ ክልሎች ውስጥ ከሁለቱ ምርጫ ክልሎች በስተቀር በሁሉም የጊዜያዊ ውጤት መለጠፉን ገልጸዋል። በሀላባ አንድ እና በቀብሪ በያ ምርጫ ክልሎች ከምርጫ ጣቢያዎች ቦታ ርቀት የተነሳ የመደመር ስራ በምርጫ ክልል ደረጃ አለመጠናቀቁን ገልጸዋል። እስከ አሁን ባለው ሂደት የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤት በማዕከል ደረጃ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ሲሆን፤ የ24 ምርጫ ክልሎች ውጤት መጽደቁን አስታውቀዋል። የ501 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ላይ ከተካሄደው ውስጥ 353 በማዕከል ደረጃ መግባቱን ገልጸው፤ በክልል ምክር ቤት ከ638 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 463 ወደ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል።
በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎች ዛሬ ድምጻቸውን ሰጥተዋል - ምርጫ ቦርድ
Jun 9, 2026 818
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች ለመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ድምጽ መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደውን ምርጫ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ቦርዱ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በመደበኛው ጠቅላላ ምርጫ በልዩ ሁኔታ ላልተሳተፉ ዜጎች የድምጽ መስጫ ቀን እንደሚያመቻች ገልጸዋል። ቦርዱ ለዚሁ የሚሆን ልዩ የምርጫ ጣቢያ በማዘጋጀት የተለያዩ ስራዎችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። ለአስፈጻሚዎች እና ለአስተባባሪዎች ስልጠና መስጠቱን ገልጸው፤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማድረጉንም ተናግረዋል። ምርጫውን ለማካሄድም በእነዚህ የምርጫ ጣቢያዎች በትላንትናው እለት የምርጫ ቁሳቁስ ሙሉ በሙሉ መቅረቡን ተናግረዋል። በካምፖች በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ሰዓትም በሁሉም ወታደራዊ ካምፖች እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ መጠለያዎች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሲካሄድ የቆየው ምርጫ ከአንድ ጣቢያ ውጪ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ገልጸው፤ በድምጽ አሰጣጥ ሂደቱም ያጋጠመ ችግር እንደሌለ ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች የስበት ማዕከልነቷን እያረጋገጠች ትገኛለች -ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 9, 2026 715
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ከተማ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች የስበት ማዕከልነቷን እያረጋገጠች ትገኛለች ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ ከጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና ከአፍሪካ በሽታዎች ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዦን ካሴያ ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። ውይይታቸውም በቀጣይ ኖቬምበር ወር አዲስ አበባ 5ኛውን አለምአቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ ለማስተናገድ መመረጧንና ኮንፈረንሱን በጋራ ለማዘጋጀት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ መሆኑን አንስተዋል። አዲስ አበባ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በመሰረተ ልማት ስራዎች፣ በነዋሪዎች እንግዳ ተቀባይነት፣ ሰላሟ የተረጋገጠ ከተማ በመሆኗ እና የተለያዩ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች ለማካሄድ ምቹ ከተማ መሆን መቻሏንም ገልጸዋል። በዚህም “የአፍሪካ የጤና ሉዓላዊነት እና ደህንነትን ማላቅ በሚል 5ኛውን ዓለም ዓቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ ለማዘጋጀት የሚያስችሉ ዝግጅቶች በስፋት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ኮንፈረንሱ የሀገራት መሪዎች፣ ሚኒስትሮች፣ የህብረተሰብ ጤና መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች እና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ትልቅ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ መሆኑንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ እና ማላዊ አቻ ተለያዩ
Jun 9, 2026 545
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ አቻው ባደረገው ሁለተኛ ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይቷል። ማምሻውን በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አዴፖጁ ባባቱንቴ በ19ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል ማላዊ መሪ ሆናለች። ቢንያም በላይ በ42ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። ጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር ተደርጎበታል። ሁለቱ ሀገራት ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በፍጹም ጥላሁን ጎል 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ዋልያዎቹ ጨዋታዎቹን ያደረጉት፣ የፊፋ ዓለም አቀፍ የብሔራዊ ቡድኖች የጨዋታ ቀናትን (FIFA Window) በመጠቀም መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አማራጮች ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው
Jun 9, 2026 665
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት ዘመን አፈራሽ የቴክኖሎጂ አማራጮች ጥቅም ላይ እየዋሉ መሆኑን የከተማና መሰረት ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እጅግ ዘመናዊና ፈጣን የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በመጠቀም የተገነቡ ቤቶችን በሚያሳይ የግንባታ ሳይት ጉብኝት አድርገዋል። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በጉብኝቱ ወቅት የተገነቡ ቤቶችን የግንባታ ሂደት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም በአሁኑ ወቅት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሪነት ከተሞች የብልጽግና ማዕከል እንዲሆኑ እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በአዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 76 የኢትዮጵያ ከተሞች ተደራሽ መሆኑን ጠቁመዋል። መንግሥት ይፋ ያደረገውን 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶች የመገንባት እቅድ ለማሳካት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ ግንባታዎችን በተለመደው መንገድ ብቻ ማከናወን የሕዝቡን የቤት ፍላጎት በፍጥነት መመለስ እንደማያስችል ጠቁመው ሚኒስቴሩ የተለያዩ አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በአጭር ጊዜ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ቤቶች መገንባት የሚያስችል የ '3D Concrete Printing' (በሮቦት የታገዘ የኮንክሪት ሕንጻ ህትመት) ቴክኖሎጂ እየተተገበረ እንደሆነ አንስተዋል። ይህ ቴክኖሎጂ የብረት ግብዓትን ወደ 30 በመቶ፣ ሲሚንቶን ደግሞ ከ35 በመቶ እስከ 40 በመቶ ገደማ መቀነስ የሚችልና በዋጋ ተወዳዳሪ የሆነ አማራጭ መሆኑንም ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅት ጂ+4 ቤቶች እየተገነቡ ሲሆን ዲዛይኑ እስከ 14 ወለል እና ከዛ በላይ መሄድ የሚያስችል አቅም እንዳለው ተናግረዋል። በተጨማሪም የብረት ተገጣጣሚ ቤቶች እና የቅድመ-ፋብሪካ ቴክኖሎጂዎች እንደ ተጨማሪ አማራጭ እየታዩ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ፖለቲካ
የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ይገኛል
Jun 9, 2026 1256
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ ከሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ክልሎች መካከል የ816 ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። ከዚህም መካከል የ24 የምርጫ ክልሎች ውጤቶች በቦርዱ ተረጋግጠው መጽደቃቸውም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በሰጡት መግለጫ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደው ልዩ ምርጫ መጠናቀቁንም ገልጸዋል። ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1ሺህ 139 ምርጫ ክልሎች ውስጥ ከሁለቱ ምርጫ ክልሎች በስተቀር በሁሉም የጊዜያዊ ውጤት መለጠፉን ገልጸዋል። በሀላባ አንድ እና በቀብሪ በያ ምርጫ ክልሎች ከምርጫ ጣቢያዎች ቦታ ርቀት የተነሳ የመደመር ስራ በምርጫ ክልል ደረጃ አለመጠናቀቁን ገልጸዋል። እስከ አሁን ባለው ሂደት የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤት በማዕከል ደረጃ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ሲሆን፤ የ24 ምርጫ ክልሎች ውጤት መጽደቁን አስታውቀዋል። የ501 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ላይ ከተካሄደው ውስጥ 353 በማዕከል ደረጃ መግባቱን ገልጸው፤ በክልል ምክር ቤት ከ638 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 463 ወደ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል።
በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎች ዛሬ ድምጻቸውን ሰጥተዋል - ምርጫ ቦርድ
Jun 9, 2026 818
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች ለመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ድምጽ መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደውን ምርጫ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ቦርዱ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በመደበኛው ጠቅላላ ምርጫ በልዩ ሁኔታ ላልተሳተፉ ዜጎች የድምጽ መስጫ ቀን እንደሚያመቻች ገልጸዋል። ቦርዱ ለዚሁ የሚሆን ልዩ የምርጫ ጣቢያ በማዘጋጀት የተለያዩ ስራዎችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። ለአስፈጻሚዎች እና ለአስተባባሪዎች ስልጠና መስጠቱን ገልጸው፤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማድረጉንም ተናግረዋል። ምርጫውን ለማካሄድም በእነዚህ የምርጫ ጣቢያዎች በትላንትናው እለት የምርጫ ቁሳቁስ ሙሉ በሙሉ መቅረቡን ተናግረዋል። በካምፖች በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ሰዓትም በሁሉም ወታደራዊ ካምፖች እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ መጠለያዎች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሲካሄድ የቆየው ምርጫ ከአንድ ጣቢያ ውጪ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ገልጸው፤ በድምጽ አሰጣጥ ሂደቱም ያጋጠመ ችግር እንደሌለ ጠቁመዋል።
በአፋር ክልል በሚገኙ ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች ድምፃቸውን እየሰጡ ነው
Jun 9, 2026 681
ሰመራ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በሚገኙ ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች ድምፃቸውን እየሰጡ መሆኑን በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኀላፊ ጣሃ ዓሊ ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለያዩ ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ወይም በልዩ ሁኔታዎች በታቀደው መደበኛ የድምፅ መስጫ ቀን መሳተፍ ላልቻሉ ዜጎች የተራዘመ ወይም ልዩ የድምፅ መስጫ ቀን ያመቻቻል። ይህ አሠራር ማንኛውም ድምፅ የመስጠት መብት ያለው ዜጋ ከዴሞክራሲያዊ ሂደቱ እንዳይገለልና የምርጫው አካታችነት እንዲረጋገጥ ይረዳል። ቦርዱ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ልዩ የድምፅ መስጫ ቀናትን በማመቻቸት ዜጎች ድምጽ እንዲሰጡ ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህም መሰረት በሀገር ውስጥ በሚገኙ መጠለያዎችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም ዜጎች ድምፅ እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል። በዚህ ጉዳይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኀላፊ ጣሃ ዓሊ እንደገለጹት፤ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ዛሬ ድምጽ እየተሰጠ ነው። መራጭ ዜጎችም ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በክልሉ ባሉ 19 ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምጽ እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። በዱብቲ፣ ገዋኔ፣ አሚባራና ገለአሎ ምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ አስራ ዘጠኝ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እየተካሄደ መሆኑንም አስታውቀዋል። በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎቹ የሚገኙ ዜጎችም ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም የሚፈልጉትን ፓርቲ በመምረጥ ላይ እንደሚገኙ አቶ ጣሃ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበር ጉዳይ ላይ አቋማችን የጸና ነው-የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jun 9, 2026 623
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበርና ሉዓላዊነቷን የማስጠበቅ ጉዳይ ላይ አቋማችን የጸና ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ታሪክ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም የተቃረኑ ባንዳዎች ሁሉ ከስመዋል፤አሁን ያሉትም የሚገጥማቸው ዕጣ ፈንታ ተመሳሳይ ይሆናል ብለዋል። የሀገርን ሉዓላዊነት ማስከበር፣የግዛት አንድነትን መጠበቅ እና የውስጥ ሰላምን ማስፈን እንደ ዋና ብሔራዊ ጥቅም የሚወሰድ መሆኑ ይታወቃል። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንኑ ለማስከበር እና ለማስጠበቅ በቁርጠኝነት እየሠራ ይገኛል። በአንድ ወቅት የባሕር በር የነበራት ኢትዮጵያ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የባሕር በር እንድታጣ የተደረገበት ሁኔታ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል። በዚህ ረገድ መንግሥት ጠንካራ የዲፕሎማሲ ጥረት እያደረገ ሲሆን ዜጎችም መሠረታዊ አጀንዳቸው አድርገውት ለምላሹ እየተሠራ መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ በተቃራኒ አንዳንዶች ከባዕዳን ጋር በመሰለፍ በባንዳነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን የሚጻረሩ እንዳሉ የሚታወቅ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ በኢትዮጵያ ታሪክ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በመቃረን የሚቆሙ ባንዳዎች መኖራቸውን አስታውሰዋል። እነዚህ አካላት የከሰሙ መሆኑን አንስተው፥ አሁን ያሉትም የሚገጥማቸው ዕጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊ እና የኢዜማ ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ታሪኩ ድንበሩ፤ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ለድርድር የሚቀርብ መሆን የለበትም ብለዋል። በመሆኑም ሁላችንም የሀገር ሰላምን በጋራ የመጠበቅ፣ የኢኮኖሚ ልማት ሥራዎችን በጋራ ማስቀጠል እና ከውጭ የሚቃጡ ጥቃቶችን በጋራ የመመከት ግዴታ አለብን ብለዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበርና ሉዓላዊነቷን የማስጠበቅ ጉዳይ ላይ የሁላችንም አቋማችን የጸና ነው ሲሉ ተናግረዋል። የነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ኡመር አብዱራህማን፤ የትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ የሚፎካከረው ከምንም በላይ ለሀገር እና ለሕዝብ ጥቅም ለመሥራት መሆን አለበት ብለዋል። ከዚህ በተቃራኒ በመቆም በሀገር ብሔራዊ ጥቅምና በዜጎች ደኅንነት ላይ መሥራት የባንዳነት ተግባር ስለመሆኑ ተናግረዋል። የሕዳሴ ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ሱራፌል እሸቱ፤ የትኛውም የፖለቲካ ተዋናይ ይሁን ዜጋ በብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ የተለየ አቋም መያዝ ተገቢነት የሌለው መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በመሆኑም የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ጨምሮ ሌሎችም ኢትዮጵያን በሚመለከቱ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ አቋማችን የጸና እና የማይናወጥ ነው ብለዋል።
የሀገራችንን ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን በመጠቀም ድምፃችንን ሰጥተናል-የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አባላት
Jun 9, 2026 627
ሰመራ፣ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ) የሀገራችንን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን፣ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን በመጠቀም ድምፃችንን ሰጥተናል ሲሉ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አባላት ገለፁ። በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ ማንኛውም መራጭ ድምፅ ለመስጠት በሚኖርበት ወይም በቋሚነት በሚሠራበት አካባቢ ተመዝግቦ መምረጥ እንዳለበት ይደነግጋል። ሆኖም ግን፣በተለያዩ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ምክንያቶች የተፈናቀሉ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች ውስጥ የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩበት ሁኔታ ይፈጠራል። ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን ያደራጃል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም በልዩ ሁኔታ ላይ ባሉ በሀገር ውስጥ መጠለያ ሊሚገኙና በመከላከያ ካምፖች ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ በመካሄድ ላይ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የሰሜን ምስራቅ ዕዙ አባላት እንዳሉት፥ ሰራዊቱ በታላቅ ጀግንነት የሀገሩን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር በማስከበር ላይ ይገኛል። ከዚህ ጎን ለጎን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ለሀገር ይበጃል ላሉት ፓርቲ ድምፃቸውን ሰጥተዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል የሰሜን ምሰራቅ ዕዝ ኦዲት ኀላፊ ተወካይ ሻለቃ ንጋቱ ኩምሳ፤ ሰራዊቱ በላቀ ጀግንነት የሀገሩን ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን በዛሬው ዕለት በመምረጡ ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል። በቀጣይነትም በምርጫው ካሸናፊው ፓርቲ ጎን በመሆን የኢትዮጵያን ሰላም የማረጋገጥ፣ ዳር ድንበርን በቆራጥነት የማስከበር ሚናችንን እንወጣለን ብለዋል። ሻለቃ ባሻ አባተ አርሲኖ በበኩላቸው፤ የተሰጠንን ሀገራዊ ግዳጅ ለመወጣትና የሀገራችንን ዳር ድንበር ለማስከበር የምንጊዜም ዝግጁነታቸውን ገልፀው፤ ከዚሁ ጎን ለጎን በምርጫው መሳተፍ በመቻላቸው እንዳስደሰታቸው ነው ያስረዱት። በምርጫው በመሳተፋቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው፤ ይህም ለሶስተኛ ጊዜያቸው መሆኑንም ተናግረዋል። መቶ ዓለቃ ኢያሱ ጩማ፤ የሀገሬን ዳር ድንበር እያስከበርኩ በዚህ ወቅት ዴሞክራሲያዊ መብቴን ተጠቅሜ መምረጥ በመቻሌ ደስተኛ ነኝ ብለዋል። 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በነፃነት መምረጥ መቻላቸውን የተናገሩት ደግሞ አስር ዓለቃ ታመነ ተሻለ ናቸው። የሀገሬን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር እየጠበቅኩና ሰላሟን እያስቀጠልኩ ከዚህ ጎን ለጎን መምረጥ በመቻሌ ደስ ብሎኛል ብለዋል።
በክልሉ በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል
Jun 9, 2026 654
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦በከፍተኛ ትጋትና የአመራር ቁርጠኝነት የተመዘገቡ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የሰላም ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ። የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ከክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ጋር በቀጣይ ስራዎች ላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል። በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በክልሉ ባለፉት ጊዜያት በከፍተኛ ትጋትና የአመራር ቁርጠኝነት በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልፀዋል። በቀጣይም በልማት፣መልካም አስተዳደር ሰላም፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል። ለሕዝብ የገባነውን ቃል በተግባር ለማረጋገጥ አመራሩ በላቀ ቁርጠኝነት ሊሠራ ይገባልም ነው ያሉት። እውነተኛ ዴሞክራሲን ከተጨባጭ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የሰላም ስኬቶች ጋር በማጣመር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና በተግባር የማረጋገጥ ስኬታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም በከፍተኛ ትጋትና ቁርጠኝነት የተመዘገቡ የልማት፣የመልካም አስተዳደርና የሰላም ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል አመራሩ የአገልጋንነት መንፈስ በመላበስ ሊያገለግል ይገባል ብለዋል። በተለይም የወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ፣የኑሮ ውድነቱን የማረጋጋት እና የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሥራ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት የሚሰሩ ስራዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ወገኖች ድምጽ እየሰጡ ነው
Jun 9, 2026 648
ደብረብርሃን፤ ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፡- በደብረ ብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ወገኖች ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ እየሰጡ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ማካሄዱ ይታወቃል። ቦርዱ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 17 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በመደበኛው ጠቅላላ ምርጫ በልዩ ሁኔታ ላልተሳተፉ ዜጎች ደግሞ የድምጽ መስጫ ቀን የሚያመቻች መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም በሀገር ውስጥ በጊዜያዊ መጠለያዎችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም ዜጎች ድምፅ እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። በዚሁ መሰረትም በደብረ ብርሃን ከተማ በሶስት በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ወገኖች ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዛሬው እለት ከማለዳው ጀመሮ ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ። በጊዜያዊ የመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎችም ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ይበጀናል የሚሉትን ፓርቲ በነጻነት እየመረጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን እና የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ
Jun 9, 2026 765
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን እና የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 24ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በዚህም የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምፅ አጽድቋል። ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳቡን ለምክር ቤቱ ያቀረቡት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ ረቂቅ አዋጁ የኮንትሮባንድ ንግድን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በጉልህ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በዘርፉ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር የተጣጣመ እና በጉምሩክ አሠራር ውስጥም ፍትሐዊነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቁመዋል። እንዲሁም እያደገ የመጣውን የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት የሚደግፍና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸው ረቂቅ አዋጁን ምክር ቤቱ እንዲያጸድቀው ጠይቀዋል። የምክር ቤቱ አባላት ረቂቅ አዋጁ በነባሩ አዋጅ ውስጥ በአተገባበር ላይ ይታዩ የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም ኮንትሮባንድን በመከላከል ሕጋዊነትን የሚያሰፍን መሆኑን ጠቁመዋል። ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን፣ አዋጅ ቁጥር 1425/2018 አድርጎ በአብላጫ ድምፅ አጽድቆታል። ምክር ቤቱ በቀጣይም የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ ላይ ተወያይቷል። ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳቡን ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) በረቂቅ አዋጁ ላይ ከሚመለከታቸው የመንግሥትና የግል ተቋማት ጋር ሰፊ ውይይት መደረጉን ተናግረዋል። የሳይበር ጥቃት የሚያስከትለው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው ቁልፍ የመሠረተ ልማት ተቋማት ከፍተኛ ጥበቃ እንደሚያስፈልጋቸው አንስተዋል። ረቂቅ አዋጁ የሕግ እና የፖሊሲ ክፍተቶችን የሚሞላ እና ቁልፍ የመሠረተ ልማቶችን በመጠበቅ ላይ ግልጽ ኃላፊነትን እና ተጠያቂነትን የሚያሰፍን መሆኑን ተናግረዋል። ምክር ቤቱ የረቂቅ አዋጁን አስፈላጊነት እና ለሀገር ሉዓላዊነት ያላቸውን ሚና በመረዳት እንዲያጸድቅ ጠይቀዋል። የምክር ቤቱ አባላት አዋጁ ለኢትዮጵያ ወሳኝ እና የሳይበር ጥቃት የሚያስከትለውን ጉዳት መቀነስ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም የነበረው አዋጅ ተጠያቂነትን የሚያሰፍን እንዳልነበር ገልጸው ረቂቅ አዋጁ ይህንን ክፍተት የሚሞላ መሆኑን ተናግረዋል። ቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሀገር ደኅንነት ሕልውና መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴው በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1426/2018 አድርጎ በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል።
ፖለቲካ
የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ይገኛል
Jun 9, 2026 1256
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ ከሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ክልሎች መካከል የ816 ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብቶ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። ከዚህም መካከል የ24 የምርጫ ክልሎች ውጤቶች በቦርዱ ተረጋግጠው መጽደቃቸውም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በሰጡት መግለጫ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደው ልዩ ምርጫ መጠናቀቁንም ገልጸዋል። ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1ሺህ 139 ምርጫ ክልሎች ውስጥ ከሁለቱ ምርጫ ክልሎች በስተቀር በሁሉም የጊዜያዊ ውጤት መለጠፉን ገልጸዋል። በሀላባ አንድ እና በቀብሪ በያ ምርጫ ክልሎች ከምርጫ ጣቢያዎች ቦታ ርቀት የተነሳ የመደመር ስራ በምርጫ ክልል ደረጃ አለመጠናቀቁን ገልጸዋል። እስከ አሁን ባለው ሂደት የ816 ምርጫ ክልሎች ውጤት በማዕከል ደረጃ የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ ሲሆን፤ የ24 ምርጫ ክልሎች ውጤት መጽደቁን አስታውቀዋል። የ501 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ላይ ከተካሄደው ውስጥ 353 በማዕከል ደረጃ መግባቱን ገልጸው፤ በክልል ምክር ቤት ከ638 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 463 ወደ ማዕከል መግባቱን ተናግረዋል።
በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎች ዛሬ ድምጻቸውን ሰጥተዋል - ምርጫ ቦርድ
Jun 9, 2026 818
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በ442 ወታደራዊ ካምፖች እና በ82 መጠለያ ጣቢያዎች ለመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ድምጽ መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ገለጹ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ በዛሬው እለት በወታደራዊ ካምፖች እና መጠለያ ጣቢያዎች የተካሄደውን ምርጫ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ቦርዱ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በመደበኛው ጠቅላላ ምርጫ በልዩ ሁኔታ ላልተሳተፉ ዜጎች የድምጽ መስጫ ቀን እንደሚያመቻች ገልጸዋል። ቦርዱ ለዚሁ የሚሆን ልዩ የምርጫ ጣቢያ በማዘጋጀት የተለያዩ ስራዎችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። ለአስፈጻሚዎች እና ለአስተባባሪዎች ስልጠና መስጠቱን ገልጸው፤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማድረጉንም ተናግረዋል። ምርጫውን ለማካሄድም በእነዚህ የምርጫ ጣቢያዎች በትላንትናው እለት የምርጫ ቁሳቁስ ሙሉ በሙሉ መቅረቡን ተናግረዋል። በካምፖች በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድምጻቸውን መስጠታቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ሰዓትም በሁሉም ወታደራዊ ካምፖች እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ መጠለያዎች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሲካሄድ የቆየው ምርጫ ከአንድ ጣቢያ ውጪ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ገልጸው፤ በድምጽ አሰጣጥ ሂደቱም ያጋጠመ ችግር እንደሌለ ጠቁመዋል።
በአፋር ክልል በሚገኙ ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች ድምፃቸውን እየሰጡ ነው
Jun 9, 2026 681
ሰመራ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል በሚገኙ ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች ድምፃቸውን እየሰጡ መሆኑን በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኀላፊ ጣሃ ዓሊ ገለፁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለያዩ ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ወይም በልዩ ሁኔታዎች በታቀደው መደበኛ የድምፅ መስጫ ቀን መሳተፍ ላልቻሉ ዜጎች የተራዘመ ወይም ልዩ የድምፅ መስጫ ቀን ያመቻቻል። ይህ አሠራር ማንኛውም ድምፅ የመስጠት መብት ያለው ዜጋ ከዴሞክራሲያዊ ሂደቱ እንዳይገለልና የምርጫው አካታችነት እንዲረጋገጥ ይረዳል። ቦርዱ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ልዩ የድምፅ መስጫ ቀናትን በማመቻቸት ዜጎች ድምጽ እንዲሰጡ ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህም መሰረት በሀገር ውስጥ በሚገኙ መጠለያዎችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም ዜጎች ድምፅ እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል። በዚህ ጉዳይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኀላፊ ጣሃ ዓሊ እንደገለጹት፤ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ዛሬ ድምጽ እየተሰጠ ነው። መራጭ ዜጎችም ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀም ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በክልሉ ባሉ 19 ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምጽ እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል። በዱብቲ፣ ገዋኔ፣ አሚባራና ገለአሎ ምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ አስራ ዘጠኝ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እየተካሄደ መሆኑንም አስታውቀዋል። በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎቹ የሚገኙ ዜጎችም ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም የሚፈልጉትን ፓርቲ በመምረጥ ላይ እንደሚገኙ አቶ ጣሃ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበር ጉዳይ ላይ አቋማችን የጸና ነው-የፖለቲካ ፓርቲዎች
Jun 9, 2026 623
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበርና ሉዓላዊነቷን የማስጠበቅ ጉዳይ ላይ አቋማችን የጸና ነው ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ። በኢትዮጵያ ታሪክ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም የተቃረኑ ባንዳዎች ሁሉ ከስመዋል፤አሁን ያሉትም የሚገጥማቸው ዕጣ ፈንታ ተመሳሳይ ይሆናል ብለዋል። የሀገርን ሉዓላዊነት ማስከበር፣የግዛት አንድነትን መጠበቅ እና የውስጥ ሰላምን ማስፈን እንደ ዋና ብሔራዊ ጥቅም የሚወሰድ መሆኑ ይታወቃል። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንኑ ለማስከበር እና ለማስጠበቅ በቁርጠኝነት እየሠራ ይገኛል። በአንድ ወቅት የባሕር በር የነበራት ኢትዮጵያ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የባሕር በር እንድታጣ የተደረገበት ሁኔታ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል። በዚህ ረገድ መንግሥት ጠንካራ የዲፕሎማሲ ጥረት እያደረገ ሲሆን ዜጎችም መሠረታዊ አጀንዳቸው አድርገውት ለምላሹ እየተሠራ መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ በተቃራኒ አንዳንዶች ከባዕዳን ጋር በመሰለፍ በባንዳነት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን የሚጻረሩ እንዳሉ የሚታወቅ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ በኢትዮጵያ ታሪክ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በመቃረን የሚቆሙ ባንዳዎች መኖራቸውን አስታውሰዋል። እነዚህ አካላት የከሰሙ መሆኑን አንስተው፥ አሁን ያሉትም የሚገጥማቸው ዕጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊ እና የኢዜማ ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ታሪኩ ድንበሩ፤ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ በየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ለድርድር የሚቀርብ መሆን የለበትም ብለዋል። በመሆኑም ሁላችንም የሀገር ሰላምን በጋራ የመጠበቅ፣ የኢኮኖሚ ልማት ሥራዎችን በጋራ ማስቀጠል እና ከውጭ የሚቃጡ ጥቃቶችን በጋራ የመመከት ግዴታ አለብን ብለዋል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበርና ሉዓላዊነቷን የማስጠበቅ ጉዳይ ላይ የሁላችንም አቋማችን የጸና ነው ሲሉ ተናግረዋል። የነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ኡመር አብዱራህማን፤ የትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ የሚፎካከረው ከምንም በላይ ለሀገር እና ለሕዝብ ጥቅም ለመሥራት መሆን አለበት ብለዋል። ከዚህ በተቃራኒ በመቆም በሀገር ብሔራዊ ጥቅምና በዜጎች ደኅንነት ላይ መሥራት የባንዳነት ተግባር ስለመሆኑ ተናግረዋል። የሕዳሴ ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ሱራፌል እሸቱ፤ የትኛውም የፖለቲካ ተዋናይ ይሁን ዜጋ በብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ የተለየ አቋም መያዝ ተገቢነት የሌለው መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በመሆኑም የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ጨምሮ ሌሎችም ኢትዮጵያን በሚመለከቱ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ አቋማችን የጸና እና የማይናወጥ ነው ብለዋል።
የሀገራችንን ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን በመጠቀም ድምፃችንን ሰጥተናል-የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አባላት
Jun 9, 2026 627
ሰመራ፣ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ) የሀገራችንን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን፣ ዴሞክራሲያዊ መብታችንን በመጠቀም ድምፃችንን ሰጥተናል ሲሉ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አባላት ገለፁ። በኢፌዴሪ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሠረት፣ ማንኛውም መራጭ ድምፅ ለመስጠት በሚኖርበት ወይም በቋሚነት በሚሠራበት አካባቢ ተመዝግቦ መምረጥ እንዳለበት ይደነግጋል። ሆኖም ግን፣በተለያዩ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ምክንያቶች የተፈናቀሉ ዜጎች እና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ ግንባሮችና ካምፖች ውስጥ የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በመደበኛው የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ለመስጠት የሚቸገሩበት ሁኔታ ይፈጠራል። ይህን መሠረታዊ መብት ለማስከበርና የምርጫውን አካታችነት ለማረጋገጥ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልዩ መመሪያዎችን በማውጣት ልዩ የምርጫ ጣቢያዎችን ያደራጃል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም በልዩ ሁኔታ ላይ ባሉ በሀገር ውስጥ መጠለያ ሊሚገኙና በመከላከያ ካምፖች ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ በመካሄድ ላይ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት የሰሜን ምስራቅ ዕዙ አባላት እንዳሉት፥ ሰራዊቱ በታላቅ ጀግንነት የሀገሩን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር በማስከበር ላይ ይገኛል። ከዚህ ጎን ለጎን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ለሀገር ይበጃል ላሉት ፓርቲ ድምፃቸውን ሰጥተዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል የሰሜን ምሰራቅ ዕዝ ኦዲት ኀላፊ ተወካይ ሻለቃ ንጋቱ ኩምሳ፤ ሰራዊቱ በላቀ ጀግንነት የሀገሩን ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን በዛሬው ዕለት በመምረጡ ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል። በቀጣይነትም በምርጫው ካሸናፊው ፓርቲ ጎን በመሆን የኢትዮጵያን ሰላም የማረጋገጥ፣ ዳር ድንበርን በቆራጥነት የማስከበር ሚናችንን እንወጣለን ብለዋል። ሻለቃ ባሻ አባተ አርሲኖ በበኩላቸው፤ የተሰጠንን ሀገራዊ ግዳጅ ለመወጣትና የሀገራችንን ዳር ድንበር ለማስከበር የምንጊዜም ዝግጁነታቸውን ገልፀው፤ ከዚሁ ጎን ለጎን በምርጫው መሳተፍ በመቻላቸው እንዳስደሰታቸው ነው ያስረዱት። በምርጫው በመሳተፋቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው፤ ይህም ለሶስተኛ ጊዜያቸው መሆኑንም ተናግረዋል። መቶ ዓለቃ ኢያሱ ጩማ፤ የሀገሬን ዳር ድንበር እያስከበርኩ በዚህ ወቅት ዴሞክራሲያዊ መብቴን ተጠቅሜ መምረጥ በመቻሌ ደስተኛ ነኝ ብለዋል። 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በነፃነት መምረጥ መቻላቸውን የተናገሩት ደግሞ አስር ዓለቃ ታመነ ተሻለ ናቸው። የሀገሬን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር እየጠበቅኩና ሰላሟን እያስቀጠልኩ ከዚህ ጎን ለጎን መምረጥ በመቻሌ ደስ ብሎኛል ብለዋል።
በክልሉ በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል
Jun 9, 2026 654
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦በከፍተኛ ትጋትና የአመራር ቁርጠኝነት የተመዘገቡ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የሰላም ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ። የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ከክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ጋር በቀጣይ ስራዎች ላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል። በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በክልሉ ባለፉት ጊዜያት በከፍተኛ ትጋትና የአመራር ቁርጠኝነት በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልፀዋል። በቀጣይም በልማት፣መልካም አስተዳደር ሰላም፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል። ለሕዝብ የገባነውን ቃል በተግባር ለማረጋገጥ አመራሩ በላቀ ቁርጠኝነት ሊሠራ ይገባልም ነው ያሉት። እውነተኛ ዴሞክራሲን ከተጨባጭ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የሰላም ስኬቶች ጋር በማጣመር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና በተግባር የማረጋገጥ ስኬታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም በከፍተኛ ትጋትና ቁርጠኝነት የተመዘገቡ የልማት፣የመልካም አስተዳደርና የሰላም ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል አመራሩ የአገልጋንነት መንፈስ በመላበስ ሊያገለግል ይገባል ብለዋል። በተለይም የወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ፣የኑሮ ውድነቱን የማረጋጋት እና የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሥራ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት የሚሰሩ ስራዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ወገኖች ድምጽ እየሰጡ ነው
Jun 9, 2026 648
ደብረብርሃን፤ ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፡- በደብረ ብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ወገኖች ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ እየሰጡ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ማካሄዱ ይታወቃል። ቦርዱ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 17 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በመደበኛው ጠቅላላ ምርጫ በልዩ ሁኔታ ላልተሳተፉ ዜጎች ደግሞ የድምጽ መስጫ ቀን የሚያመቻች መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም በሀገር ውስጥ በጊዜያዊ መጠለያዎችና በወታደራዊ ካምፖች ልዩ ጣቢያዎችን በማቋቋም ዜጎች ድምፅ እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። በዚሁ መሰረትም በደብረ ብርሃን ከተማ በሶስት በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ወገኖች ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዛሬው እለት ከማለዳው ጀመሮ ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ። በጊዜያዊ የመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎችም ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ይበጀናል የሚሉትን ፓርቲ በነጻነት እየመረጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን እና የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ
Jun 9, 2026 765
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን እና የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 24ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በዚህም የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምፅ አጽድቋል። ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳቡን ለምክር ቤቱ ያቀረቡት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ ረቂቅ አዋጁ የኮንትሮባንድ ንግድን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በጉልህ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በዘርፉ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር የተጣጣመ እና በጉምሩክ አሠራር ውስጥም ፍትሐዊነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቁመዋል። እንዲሁም እያደገ የመጣውን የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት የሚደግፍና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸው ረቂቅ አዋጁን ምክር ቤቱ እንዲያጸድቀው ጠይቀዋል። የምክር ቤቱ አባላት ረቂቅ አዋጁ በነባሩ አዋጅ ውስጥ በአተገባበር ላይ ይታዩ የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም ኮንትሮባንድን በመከላከል ሕጋዊነትን የሚያሰፍን መሆኑን ጠቁመዋል። ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን፣ አዋጅ ቁጥር 1425/2018 አድርጎ በአብላጫ ድምፅ አጽድቆታል። ምክር ቤቱ በቀጣይም የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ ላይ ተወያይቷል። ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳቡን ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) በረቂቅ አዋጁ ላይ ከሚመለከታቸው የመንግሥትና የግል ተቋማት ጋር ሰፊ ውይይት መደረጉን ተናግረዋል። የሳይበር ጥቃት የሚያስከትለው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው ቁልፍ የመሠረተ ልማት ተቋማት ከፍተኛ ጥበቃ እንደሚያስፈልጋቸው አንስተዋል። ረቂቅ አዋጁ የሕግ እና የፖሊሲ ክፍተቶችን የሚሞላ እና ቁልፍ የመሠረተ ልማቶችን በመጠበቅ ላይ ግልጽ ኃላፊነትን እና ተጠያቂነትን የሚያሰፍን መሆኑን ተናግረዋል። ምክር ቤቱ የረቂቅ አዋጁን አስፈላጊነት እና ለሀገር ሉዓላዊነት ያላቸውን ሚና በመረዳት እንዲያጸድቅ ጠይቀዋል። የምክር ቤቱ አባላት አዋጁ ለኢትዮጵያ ወሳኝ እና የሳይበር ጥቃት የሚያስከትለውን ጉዳት መቀነስ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም የነበረው አዋጅ ተጠያቂነትን የሚያሰፍን እንዳልነበር ገልጸው ረቂቅ አዋጁ ይህንን ክፍተት የሚሞላ መሆኑን ተናግረዋል። ቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሀገር ደኅንነት ሕልውና መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴው በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1426/2018 አድርጎ በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል።
ማህበራዊ
አዲስ አበባ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች የስበት ማዕከልነቷን እያረጋገጠች ትገኛለች -ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 9, 2026 715
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ከተማ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች የስበት ማዕከልነቷን እያረጋገጠች ትገኛለች ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ ከጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና ከአፍሪካ በሽታዎች ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዦን ካሴያ ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። ውይይታቸውም በቀጣይ ኖቬምበር ወር አዲስ አበባ 5ኛውን አለምአቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ ለማስተናገድ መመረጧንና ኮንፈረንሱን በጋራ ለማዘጋጀት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ መሆኑን አንስተዋል። አዲስ አበባ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በመሰረተ ልማት ስራዎች፣ በነዋሪዎች እንግዳ ተቀባይነት፣ ሰላሟ የተረጋገጠ ከተማ በመሆኗ እና የተለያዩ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች ለማካሄድ ምቹ ከተማ መሆን መቻሏንም ገልጸዋል። በዚህም “የአፍሪካ የጤና ሉዓላዊነት እና ደህንነትን ማላቅ በሚል 5ኛውን ዓለም ዓቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ ለማዘጋጀት የሚያስችሉ ዝግጅቶች በስፋት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ኮንፈረንሱ የሀገራት መሪዎች፣ ሚኒስትሮች፣ የህብረተሰብ ጤና መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች እና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ትልቅ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ መሆኑንም ገልጸዋል።
የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አማራጮች ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው
Jun 9, 2026 665
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላት ዘመን አፈራሽ የቴክኖሎጂ አማራጮች ጥቅም ላይ እየዋሉ መሆኑን የከተማና መሰረት ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እጅግ ዘመናዊና ፈጣን የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በመጠቀም የተገነቡ ቤቶችን በሚያሳይ የግንባታ ሳይት ጉብኝት አድርገዋል። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በጉብኝቱ ወቅት የተገነቡ ቤቶችን የግንባታ ሂደት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም በአሁኑ ወቅት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሪነት ከተሞች የብልጽግና ማዕከል እንዲሆኑ እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በአዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 76 የኢትዮጵያ ከተሞች ተደራሽ መሆኑን ጠቁመዋል። መንግሥት ይፋ ያደረገውን 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶች የመገንባት እቅድ ለማሳካት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ ግንባታዎችን በተለመደው መንገድ ብቻ ማከናወን የሕዝቡን የቤት ፍላጎት በፍጥነት መመለስ እንደማያስችል ጠቁመው ሚኒስቴሩ የተለያዩ አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በአጭር ጊዜ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ቤቶች መገንባት የሚያስችል የ '3D Concrete Printing' (በሮቦት የታገዘ የኮንክሪት ሕንጻ ህትመት) ቴክኖሎጂ እየተተገበረ እንደሆነ አንስተዋል። ይህ ቴክኖሎጂ የብረት ግብዓትን ወደ 30 በመቶ፣ ሲሚንቶን ደግሞ ከ35 በመቶ እስከ 40 በመቶ ገደማ መቀነስ የሚችልና በዋጋ ተወዳዳሪ የሆነ አማራጭ መሆኑንም ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅት ጂ+4 ቤቶች እየተገነቡ ሲሆን ዲዛይኑ እስከ 14 ወለል እና ከዛ በላይ መሄድ የሚያስችል አቅም እንዳለው ተናግረዋል። በተጨማሪም የብረት ተገጣጣሚ ቤቶች እና የቅድመ-ፋብሪካ ቴክኖሎጂዎች እንደ ተጨማሪ አማራጭ እየታዩ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ደኅንነቱ የተጠበቀ የትራንስፖርት ሥርዓት ለመገንባት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው
Jun 9, 2026 337
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ የትራፊክ አደጋን ለመከላከልና ደኅንነቱ የተጠበቀ የትራንስፖርት ሥርዓት ለመገንባት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የኦሮሚያ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ገለጸ። ኤጀንሲው የመንገድ ደኅንነትን የማረጋገጥ ዓላማ በዘላቂነት ለማሳካት የሚያግዝ "ብሉምበርግ ፊላንትሮፒስ" ከተሰኘ ዓለምአቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር የውይይት መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ የኦሮሚያ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ኃላፊ ከማል ማሜ እንደገለጹት፤ የመንገድ ትራፊክ ደኅንነትን ይበልጥ ለማጠናከር ከድርጅቱ ጋር እ.አ.አ ከ2026 እስከ 2030 ድረስ በጋራ መሥራት የሚያስችል ስምምነት ላይ ተደርሷል። በአሁኑ ወቅት ይህንን ስምምነት ወደ ሙሉ ትግበራ የማሸጋገር ሥራ የተጀመረ ሲሆን፣ በመጀመሪያው ምዕራፍ በሸገር፣ በቢሾፍቱና በአዳማ ከተሞች ላይ ትኩረት አድርጎ ስኬታማ በሆነ መንገድ እየተተገበረ ይገኛል። ከተቋሙ ጋር የሚደረገው ትብብር የመንገድ ደኅንነትን ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና ያላቸውን የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን፣ የቴክኒክና የቁሳቁስ አቅርቦቶችን እንዲሁም የፋይናንስ አቅም ግንባታዎችን ያካተተ መሆኑን አብራርተዋል። የትራፊክ አደጋዎችን በጋራ ለመከላከልና ደኅንነቱ የተጠበቀ የትራንስፖርት ሥርዓት ለመገንባት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎና ኃላፊነት ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የብሉምበርግ ግብረ ሰናይ ድርጅት የዓለም አቀፍ የመንገድ ደኅንነት ዳይሬክተር ኬሊ ላርሰን፣ ድርጅቱ በአዲስ አበባ የነበረውን ውጤታማ ተሞክሮ በመጠቀም በኦሮሚያ ክልልም በአደጋ ተጋላጭ ቦታዎች ላይ ያተኮረ የመረጃ ማሰባሰብና ትንተና ሥራን እንደሚደግፍ ገልጸዋል። ይህ ተነሳሽነት በአሽከርካሪዎችና እግረኞች ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ እንደ ፍጥነት መቆጣጠሪያ፣ የመቀመጫ ቀበቶና ራስ መከላከያ አጠቃቀም ባሉ የሕግ ማስከበር ሥራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የትራፊክ ፖሊሶችን አቅም የመገንባት ሥራ ያካትታል ብለዋል። ድርጅቱ የመንገድ ደኅንነትን ለማስጠበቅና አደጋዎችን ለመቀነስ የሚያደርገውን ዘርፈ-ብዙ የቴክኒክና የፋይናንስ ድጋፍ እአአ እስከ 2030 ድረስ በኢትዮጵያ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል። ፕሮጀክቱ ተግባራዊ ከሚሆንባቸው ከተሞች መካከል የሸገር ከተማ መንገድ ትራፊክ ደኅንነት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ማሙሽ ጫላ በሰጡት አስተያየት፤ በከተማዋ አስተማማኝ የመንገድ ደኅንነትን ለማስፈን በርካታ ውጤታማና ተስፋ ሰጪ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የቢሾፍቱ ከተማ የትራንስፖርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አበራ ሽፈራው በበኩላቸው፤ ደኅንነቱ የተጠበቀ የትራፊክ ሥርዓት መገንባት የሚያስችሉ የተለያዩ የሕዝብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች በስኬት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
የክልሉ መንግስት ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት ትኩረት ሰጥቷል-ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ
Jun 9, 2026 372
ጅግጅጋ ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦ የክልሉ መንግስት ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት ትኩረት መስጠቱን የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ ገለጹ፡፡ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ፤ በክልሉ ፋፈን ዞን አውበሬ ወረዳ ሼደር ከተማ የተገነባውን አዳሪ ትምህርት ቤት መርቀው በይፋ ስራ አስጀምረዋል። ርዕሰ መስተደድሩ አቶ ሙስጠፌ በወቅቱ፤ በክልሉ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማስፋት የተማረ ትውልድ ለማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ነው ብለዋል። አዳሪ ትምህርት ቤቱ ተገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑም የክልሉ መንግስት ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት የሰጠውን ትኩረት የሚያሳይ ነው ብለዋል። የሼደር ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች እና የከተማው ነዋሪዎች በበኩላቸው፤ የክልሉ መንግስት ለህዝቡ በገባው ቃል መሰረት ትምህርት ቤቱን በማስገንባት ለአገልግሎት በማብቃቱ ምስጋና አቅርበዋል። ትምህርት ቤቱ የአስተዳደር ቢሮዎችን፣ የመማሪያ ክፍሎችን፣ የተማሪዎችና የመምህራን ማረፍያ ክፍሎችን፣ ቤተ መፃሕፍት እና ሌሎች ለትምህርት አገልግሎት ጠቃሚ የሆኑ ክፍሎችን አካቶ የያዘ መሆኑ ተገልጿል። የትምህርት ቤቱ ግንባታ 138 ሚሊየን ብር ወጪ እንደተደረገበትም በወቅቱ ተገልጿል።
ኢኮኖሚ
የወልድያ ሕዝብና አመራር ለፈተና ሳይበገሩ ከተማዋን ወደ ዘመናዊ የልማት ማዕከልነት እየቀየሩ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
Jun 9, 2026 708
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ የወልድያ ከተማ ሕዝብና አመራር ሰው ሠራሽ ፈተናዎችን በጽናት በመቋቋም ከተማዋን ወደ ዘመናዊ የልማት ማዕከልነት መቀየር መቻላቸውን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ ይህንን የገለጹት በወልድያ ከተማ የተገነቡ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በበቁበት መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ ከተማዋ የጀግኖች ታሪክ የሚዘከርባት፣ ሕብረ-ብሔራዊ ወንድምና እህት ሕዝቦች በፍቅርና በአንድነት የሚኖሩባት የኢትዮጵያዊነት መገለጫ መሆኗን ገልጸዋል። ከተማዋ በተደጋጋሚ ያጋጠሟትን ፈተናዎች ተቋቁማ፣ በአንድ እጇ ሰላምን በሌላ እጇ ልማትን ይዛ መጓዟን አብራርተዋል። ዛሬ የተመረቁ የልማት ፕሮጀክቶች የወልድያ ከተማን ገጽታ የቀየሩ መሆናቸውን ነው ርዕሰ መስተዳድሩ የጠቀሱት። ታዳጊዎች ስለ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና ስለ ወደፊት ቴክኖሎጂ ያላቸው የእውቀት መሻት ከተማዋ ለነዋሪዎቿ ምቹ ከመሆን ባለፈ ራዕይ ያላቸው ዜጎችን ለመቅረጽ እየሠራች መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ በፈተና ውስጥ ሆኖ የመሥራት ልምድ ሌሎች የክልሉ ከተሞችና ወረዳዎች ሊማሩበትና የሥራ መነሻ ሊያደርጉት የሚገባ መሆኑን በአጽንኦት ጠቅሰዋል። ወልድያ ገና ብዙ ልማት እንደሚገባትና በአራቱም አቅጣጫዎች ለንግድ ምቹ የሆነ ስትራቴጂካዊ አቀማመጧን ታሳቢ ያደረገ ጉዞን ማፋጠን እንደሚገባም አንስተዋል። በሼህ መሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ የተገነባው ዘመናዊ ስታዲየም ከፍተኛ እድሳት እንደሚፈልግና ከተማዋን የስፖርትና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ለስታዲየሙ የሚመጥኑ ዘመናዊ ሆቴሎች ሊገነቡ እንደሚገባ አመላክተዋል። የከተማዋን ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ ከተቻለ ከዚህ የላቀ ልማት ማምጣት እንደሚቻልም ገልጸዋል። የወልድያ ከተማ ከንቲባ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፤ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹና ፅዱ ማድረግ ያስቻሉ አስደናቂ የልማት ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። የወልድያ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የከተማዋ ነዋሪዎች ፈጣን የመንግሥት አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር የሚፈጥር መሆኑን አስረድተዋል። በልማት ፕሮጀክቶች ምረቃ መርሃ ግብሩ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ወደፊት እየገሰገሰች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Jun 9, 2026 439
አዲስ አበባ ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ወደፊት እየገሰገሰች ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወልድያ ከተማ የተገነቡ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ከፍተዋል። በምረቃው ወቅትም እንደገለጹት የተመረቁት የልማት ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን ወደፊት የመገስገስ ጉዞ የሚያሳዩና የኢትዮጵያን ዕድገት ማንም ሊያስቆመው እንደማይችል ማረጋገጫዎች ናቸው። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የወልድያ ከተማ ሕዝብ ጽንፈኝነትንና ከፋፋይነትን በመቃወም የሚታወቅ፣ ምርጫው ሰላምና ጠንካራ መንግሥት መሆኑን በየጊዜው ማሳየቱን ገልጸዋል። መንግሥት ትግሉ ከተወሰኑ አካባቢ ሽፍቶች ጋር ሳይሆን መንገዳቸውን ክፍፍልና ድህነት ካደረጉ ቆሞ ቀር ኃይሎች ጋር መሆኑን ጠቅሰዋል። ላለፉት 50 እና 60 ዓመታት ያረጀ አስተሳሰብ ይዘው የቆሙ አካላት የሀገሪቱን ፈጣን ጉዞ መገንዘብ እንዳልቻሉም አስረድተዋል። በጫካ ያሉ አካላት የኮሪደር ልማትን፣ የሌማት ትሩፋትን፣ የገበታ ፕሮጀክቶችንና የስንዴ አብዮትን የመሰሉ በሀገሪቱ የመጡ ታላላቅ ለውጦችን ለማየት እንዳልታደሉ ገልጸዋል። በከተሞች የሚካሄደው የኮሪደር ልማት የውበት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ከተሞችን የማዘመንና የሕዝብን የኑሮ ደረጃ ከፍ የማድረግ ዓላማ በማንገብ በመስፋፋት ላይ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ከተሞች ፉክክር ከምሥራቅ አፍሪካና ከዓለም ከተሞች ጋር መሆን እንዳለበት የገለጹ ሲሆን፤ አገልግሎትን ለማዘመንም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመላ ሀገሪቱ እየተስፋፋ መሆኑን ጠቁመዋል። በወልድያ ከተማ የተገነቡት የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት፣ የዲጂታል ቤተ መጻሕፍትና የሳይንስ ካፌዎች ትውልዱን ከዕለት መረጃ ወደ ጥልቅ ዕውቀትና ምርምር የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገበያ ማዕከላትና የሱቆች ፕሮጀክቶች የንግድ እንቅስቃሴን በማሳለጥ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸውና በሌማት ትሩፋት አማካኝነትም በምግብ ራስን የመቻል ጉዞው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈችና ተስፋዎቿን እየጨበጠች መጓዟን እንደምትቀጥል የገለጹት አቶ ተመስገን፣ ጠላት ቢሰበሰብ የሀገሪቱን ጉዞ ማደናቀፍ እንደማይችል አጽንኦት ሰጥተዋል። የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ገጠር ጭምር በማስፋፋት የሀገሪቱን ብልጽግና እውን ለማድረግ መንግሥት፣ ባለሃብቱና ሕዝቡ በጋራ ሊሠሩ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በወልድያ ከተማ የልማት ፕሮጀክቶችን መረቁ
Jun 9, 2026 273
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በወልድያ ከተማ የልማት ፕሮጀክቶችን ዛሬ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው፤ የኢትዮጵያ ጉዞ ወደፊት ነው። ጠላት የፈለገውን ያህል ቢያቅድ ከጉዟችን እንደማያስቆመን ወልድያ ምስክር ናት ብለዋል። ዛሬ በታሪካዊቷ፣ በየጁዎች ሥልጣኔ መገኛ በሆነችው ወልድያ ከተማ በመገኘት፣ አመራርና ሕዝብ በአንድነት ተግቶ ያሳካቸውን የልማት ፕሮጀክቶች መመረቃቸውን ገልጸዋል። ወልድያ የልማት፣ የፅናትና የድል አምባ ናት ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተማዋን የማዘመን፣ የኮሪደር ልማትን የማስፋፋት፣ የሕዝብና የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍትን የመገንባት እንዲሁም የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከላትን እውን የማድረግ ሥራዎቻችን ወደፊት የመገስገሳችን ማረጋገጫዎች ናቸው ሲሉም ተናግረዋል። መንገዳችን መደመር፣ ግባችን ደግሞ ብልጽግና ነው! ትግላችን መንገዳቸውን ክፍፍል፣ ግባቸውን ድህነት ካደረጉ ቆሞ-ቀሮች ጋር በመሆኑ የኢትዮጵያን ልዕልና ሳናረጋግጥ አንቆምም ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው። ሺህ ጠላት ቢሰበሰብ የኢትዮጵያን ጉዞ ለአፍታም እንደማያስቆመው አስገንዝበዋል።
የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው
Jun 9, 2026 285
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ታዜር ገብረእግዚአብሔር ገለጹ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ ቁጥር 589/2018 ዓ.ም ዙሪያ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል። ይህ ሥርዓት አርሶ አደሮች፣ ማኅበራትና አቀናባሪዎች ደረጃውን የጠበቀ ምርት በመጋዘን አስቀምጠው በደረሰኝ አማካኝነት የባንክ ብድር የሚያገኙበት አሠራር ነው። አሠራሩ አርሶ አደሮች በምርት መሰብሰቢያ ወቅት የሚገጥማቸውን የገንዘብ ዕጥረት ለመቅረፍ በኢትዮጵያ ሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አማካኝነት ተግባራዊ ሆኗል። ቀደም ሲል አርሶ አደሮች በገንዘብ እጥረት ምርታቸውን በርካሽ ዋጋ ለመሸጥ ይገደዱ የነበረ ሲሆን፣ ይህም በምርታማነትና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። አዲሱ አሠራር ግን አርሶ አደሮች ምርታቸውን በደረሰኝ በማስያዝ ብድር እንዲያገኙና በተሻለ ዋጋ በመሸጥ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያሳድጉ ያስችላቸዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ታዜር ገብረእግዚአብሔር እንዳሉት፤ ሥርዓቱ የገጠርና የግብርና ልማት ሽግግርን በማፋጠን አስተማማኝ የፋይናንስ አቅርቦት ዕድል የሚፈጥር ነው። ሥርዓቱ ከ20 ዓመታት በላይ ቢያስቆጥርም ግልፅ ተቆጣጣሪ ባለመኖሩ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ግን መንግሥት በሕግና መመሪያ ባለቤት በማበጀት ተግባራዊ አድርጎታል ብለዋል። አርሶ አደሮች ምርታቸውን በአስተማማኝ ሁኔታ በማከማቸት ብድር ማግኘት እንዲሁም መቼና እንዴት መሸጥ እንዳለባቸው የማሰቢያ ጊዜ እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል። ሥርዓቱንም በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር እንዲሆን በማስቻል የፋይናንስ ተቋማትን የሚያበረታታ ደንብ፣ መምሪያና የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋቱን አስረድተዋል። የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ) የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ይኼነው ዘውዴ (ዶ/ር) የደረሰኝ ሥርዓቱ የአርሶ አደሮችን ድካም የሚመጥን የተሻለ ገበያና ዋጋ ማግኘት የሚያስችል ነው ብለዋል። አሠራሩ ምርታማነትን በማሻሻል፣ በተመዘገበ መጋዘን ለሚቀመጥ ምርት በደረሰኙ የብድር ዋስትና የሚያገኙበትን ዕድል በመፍጠር የአርሶ አደሮችን የመደራደር አቅም ያሳድጋል ብለዋል። የብድር መስፈርቶች የአርሶ አደሮችና ማኅበራትን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ማድረግ እንዳለባቸው የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ሥርዓቱ የአርሶ አደሩን ሕይወት በመቀየር የግብርና ሽግግርን ያሳካል ብለዋል። አግራ ግብርናን ለማዘመን ከአፍሪካ ሕብረት ጋር በ15 ሀገራት እየሠራ መሆኑን ገልጸው፣ ለኢትዮጵያ የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ውጤታማነትም በትብብር እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። የኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዮሐንስ አምቢሳ ፤የዕዳ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ ለባንኮች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ አርሶ አደሮችና ህብረት ሥራ ማህበረት የብድር ማስያዣ ችግር ይገጥማቸው እንደነበር ገልጸው፤ ባንኮች የደረሰኝ ሥርዓቱን ብቻ በመያዝ ብድር ማቅረብ ይችላሉ ብለዋል፡፡ የአማራ ባንክ የብድር ክፍል ኃላፊ እሸቴ የማታ፤ በበኩላቸው ባንኮች የዕዳ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓቱን እንደ ብድር ምርት ማድረጋቸው በአርሶ አደሮችና ባንኮች መካከል መተማመንን ይፈጥራል ብለዋል፡፡ የዕዳ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ ለባንኮች አስተማማኝ የማበደር ዋስትና እና ለአርሶ አደሮች ደግሞ እፎይታን እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በክልሉ አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ ህዝብን ከወጪና እንግልት ለመታደግ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ
Jun 9, 2026 555
አርባ ምንጭ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስታዊ አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ ህዝብን ከወጪና እንግልት ለመታደግ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። በአርባ ምንጭ ከተማ የተገነባው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች የተለያዩ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ እያስቻለ ነው። በክልሉም በወላይታ ሶዶ፣ በአርባ ምንጭ እና በዲላ ከተሞች ማዕከሉን ተደራሽ በማድረግ ህዝቡ ባለበት ሆኖ ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት እንዲያገኝ ለማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። በዲጂታል ሥርአት ታግዞ የሚሰጠው አገልግሎት ለዘመናዊ የመንግስት አስተዳደር ጉልህ ፋይዳ አለው ያሉት አቶ ጥላሁን፣ አገልግሎቱ ፈጣንና ከሙስና የጸዳ በመሆኑ የዜጎችን እርካታ ከፍ ያደርገዋል ብለዋል። ማዕከሉ ዜጎች ወደክልሉ የተለያዩ ከተሞች ሳይሄዱ የፌደራል ተቋማት አገልግሎቶችን ጭምር በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል። በክልሉ መንግስታዊ አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ ህዝብን ከወጪና እንግልት ለመታደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል። የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አልማዝ መሰለ በበኩላቸው ማዕከሉ ሰው ተኮር እንደሆነና በመንግስት አገልግሎት ላይ ይታዩ የነበሩ ችግሮችን በመሠረታዊነት የሚፈታ ነው ብለዋል። የተገልጋዩን ጊዜ፣ ጉልበት እና ወጪ የሚቀንስ መሆኑን ጠቅሰው፣ ውጤታማና ለዜጎች ክብር የሰጠ አገልግሎት በመሆኑ ህዝብና መንግስትን በማቀራረብ ለሀገሪቱ ብልጽግና ጉዞ ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል። "መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መንግስት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል" ያሉት ደግሞ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሙሉቀን ቀሬ ናቸው። አገልግሎቱ በዲጂታል ሥርአት የታገዘ በመሆኑ ህዝቡን በፍትሃዊነት ለማገልገል፣ መረጃን በአግባቡ ለማደራጀት እንዲሁም የተገልጋይ እንግልትን ለማስቀረት ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ413 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ መገንባቱን ገልጸዋል። በማዕከሉ የምረቃ መርሀግብር ላይ በየደረጃው ካሉ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች በተጨማሪ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል። ማዕከሉ አራት የፌደራልና አምስት የክልል ተቋማትን በአንድነት ያጣመረ ሲሆን ከ32 በላይ አገልግሎቶችም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው የሚሰጡበት መሆኑ ታውቋል።
የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 8, 2026 1195
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባዋ በመልዕክታቸው፤ ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው ብለዋል። 9ኛው አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ ዛሬ መጀመሩንም አስታውቀዋል። የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ፣ ፈጣን፣ ግልፅ እና ተደራሽ ለማድረግ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ስራ በ2018 ዓ.ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ ለማስጀመር ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። ለህዝቡ ቃል በተገባው መሰረትም የዛሬውን ጨምሮ ዘጠኝ ማዕከላትን ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ጠቁመዋል። ይህ አሰራር የአገልግሎት እንግልትን፣ ጉቦ የመጠየቅ ችግርን ለመቅረፍ፣ ተጠያቂነትን እና የህዝብን በክብር የመገልገል መብት ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ነው ያብራሩት። ህዝቡ ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜውንና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል ለማድረግ የታቀደውን ግብ በማሳካት የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ከንቲባዋ ገልጸዋል። በየካ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ላደረጉት አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል
Jun 8, 2026 800
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ። ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ በየካ ክፍለ ከተማ የተገነባውን 9ኛ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎትን መርቀው ስራ አስጀምረዋል። ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ በዚሁ ወቅት፤ የማዕከሉ መገንባት ህብረተሰቡ ፈጣን፣ ግልጽ እና ፍትሐዊ አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችል ነው ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ ቀደም ሲል ከህዝብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች የአገልግሎት አሰጣጥ ውስንነት የህዝብ እንግልትና ምሬት ምንጭ መሆናቸውን ማረጋገጥ መቻሉን አውስተዋል። ለህዝብ ጥያቄ ቅድሚያ መስጠት ዋና መገለጫ የሆነው ከተማ አስተዳደሩ፤ ጥራት ላለው የመንግሥት አገልግሎት እንቅፋት የሆኑ ምክንያቶችን ነቀሶ በማውጣት እልባት እየሰጠ መምጣቱን ተናግረዋል። በዚህም አልፎ አልፎ ይስተዋሉ የነበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት አንዱና ዋነኛው መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ የዛሬውን ጨምሮ ዘጠኝ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በማደራጀት ወደ ስራ መግባቱን ጠቅሰዋል። እነዚህ ማዕከላት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙላቸው እና የበቃ የሰው ሀይል የተሟሉላቸው መሆናቸውን ገልጸዋል። የማዕከላቱ ወደ ስራ መግባት ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበትን አሰራርን እውን በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ይነሱ የነበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን መቅረፍ ማስቻላቸውን ነው የተናገሩት። በቀጣይም በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት ዜጎችን ከእንግልትና ከአላስፈላጊ የገንዘብ ወጭ ታድጓል ብለዋል።
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የጤና ተቋማትን አገልግሎት ወረቀት አልባ የሚያደርግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ ነው
Jun 8, 2026 518
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018(ኢዜአ)፦ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የጤና ተቋማትን አገልግሎት ወረቀት አልባ የሚያደርግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ገለጹ፡፡ ዶክተር ደረጄ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ የልማት አቅጣጫ በጤናው ዘርፍ ፈጣንና ቀልጣፋ የአገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂም የጤና ተቋማትን አገልግሎት በማዘመን ወሳኝ መሰረት መጣሉን አስታውሰዋል። ለአብነትም የጤና ተቋማትን አገልግሎቶች በኦላይን የዲጂታል ሥርዓት በማሰናሰል ተገልጋዮች ቀልጣፋና ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር የኢንተርኔት አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው አካባቢ የሚገኙ ጤና ተቋማት ጭምር ''በሄልዝ ኔት'' ለማስተሳሰር መሰረት እየጣለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የዲጂታል ጤና አገልግሎቱም የበሽታ መከላከልና አክሞ ማዳን አቅሞችን በማጎልበት ረገድ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዲጂታል ጤና አገልግሎቶችን ተደራሽነት ለማስፋት በተከናወኑ ተግባራትም 40 ሶፍትዌሮችን በማልማት ተገልጋዮች የጤና መረጃና አገልግሎት እንዲያገኙና መረጃን በስፋት እንዲሰንዱ እየተደረገ መሆኑን አንሰተዋል። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የጤና ተቋማትን አገልግሎት ወረቀት አልባ የሚያደርግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል። በቀጣይም በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓት የጤና ምኅዳሩን በዲጂታላይዜሽን የአሰራር ሥርዓት በማሳለጥ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ እና ማላዊ አቻ ተለያዩ
Jun 9, 2026 545
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ አቻው ባደረገው ሁለተኛ ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይቷል። ማምሻውን በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አዴፖጁ ባባቱንቴ በ19ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል ማላዊ መሪ ሆናለች። ቢንያም በላይ በ42ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፋት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። ጨዋታው ተመጣጣኝ ፉክክር ተደርጎበታል። ሁለቱ ሀገራት ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በፍጹም ጥላሁን ጎል 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ዋልያዎቹ ጨዋታዎቹን ያደረጉት፣ የፊፋ ዓለም አቀፍ የብሔራዊ ቡድኖች የጨዋታ ቀናትን (FIFA Window) በመጠቀም መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዩጋንዳ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ያደርጋል
Jun 9, 2026 252
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዩጋንዳ አቻው ጋር ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የወዳጅነት ጨዋታውን ያከናውናል። ዓለም አቀፍ የወዳጅነት መርሐ ግብሩ ብሔራዊ ቡድኑ በዓለም ዋንጫ የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ ከዛምቢያ ጋር ለሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ዝግጅት የሚያግዝ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ጨዋታው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይካሄዳል። አሰልጣኝ ራውዳ ዓሊ ከዛምቢያ ጋር ለሚደረገው ወሳኝ ጨዋታ ዝግጅት ትናንት ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ ማድረጋቸው ይታወቃል። ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ነገ በካፍ የልህቀት ማዕከል በመሰባሰብ ዝግጅት ማድረግ እንደሚጀምሩ ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዛምቢያ ጋር የመጨረሻ ዙር የማጣሪያ ጨዋታውን ሰኔ 27 እና ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ያደርጋል። ኢትዮጵያ በድምር ውጤት ካሸነፈች በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ታልፋለች። 10ኛው የፊፋ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ ከማላዊ ጋር ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታዋን ታደርጋለች
Jun 9, 2026 373
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ አቻው ጋር ሁለተኛውን ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታውን ዛሬ ያካሂዳል። ጨዋታው ምሽት 12 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም ይከናወናል። ሁለቱ ሀገራት ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ በፍጹም ጥላሁን ጎል 1 ለ 0 አሸንፋለች። ይህ ውጤት ኢትዮጵያ ከአምስት ዓመታት በኋላ በማላዊ ላይ ያስመዘገበችው ድል ነው። ኢትዮጵያ እና ማላዊ ከቀናት በፊት የተደረገውን የወዳጅነት ጨዋታ ጨምሮ 15 ጊዜ ተገናኝተዋል። ሁለቱም ቡድኖች በተመሳሳይ አምስት ጊዜ ሲያሸንፉ በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ወጥተዋል። ኢትዮጵያ በጨዋታዎቹ ላይ 17 ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ ማላዊ 14 ጎሎችን አስቆጥራለች። ብሔራዊ ቡድኖቹ ከዛሬው ጨዋታ በፊት የመጨረሻ ልምምዳቸውን ትናንት በድሬዳዋ ስታዲየም አከናውነዋል። የኢትዮጵያ ተጫዋቾች በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ዋልያዎቹ ጨዋታዎቹን እያደረጉ የሚገኙት፣ የፊፋ ዓለም አቀፍ የብሔራዊ ቡድኖች የጨዋታ ቀናትን (FIFA Window) በመጠቀም መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
በሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ ተደረገ
Jun 8, 2026 653
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ራውዳ ዓሊ፣ ቡድኑ በዓለም ዋንጫ የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ ከዛምቢያ አቻው ጋር ለሚያደርገው ወሳኝ ጨዋታ ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርበዋል። ከተመረጡት ተጫዋቾች መካከል ግብ ጠባቂዎቹ መቲ ረታ (ልደታ ክፍለ ከተማ) ፣ ኑዳ ሁሴን (አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ) እና ባንቺጊዜ አንተነህ (ኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ) ጥሪ ደርሷቸዋል። ማንጠግቦሽ አድማሱ (አርባምንጭ ከተማ )፣ እየሩሳሌም ኤርሚያስ (መቀሌ 70 እንደርታ)፣ ኤልሻዳይ ዮሴፍ ( ጉለሌ ክፍለ ከተማ) ፣ ቤተልሄም ጌታቸው (ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ)፣ መድኃኒት አለሙ (አርባምንጭ ከተማ)፣ መክሊት መሰለ (ጉለሌ ክፍለ ከተማ) እና ዝናሽ ሰለሞን (ድሬዳዋ ከተማ) በተከላካይ መስመር የሚገኙ ተጫዋቾች ናቸው። በአማካይ ክፍል ናጆክ ዱክ ( የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ)፣ ሊያም ዳንኤል (የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ)፣ ጌጤነሽ ተስፋዬ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ)፣ ቢታኒያ አስተረፍ (ሲዳማ ቡና) ፣ ናግዋ ማን (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ)፣ ኮከብ ደጀኔ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ)፣ ኤልሳ መኮንን (ድሬዳዋ ከተማ) እና ሊዲያ ሰለሞን (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ) በጥሪው ተካትተዋል። ምህረት ወሰኑ (ሸገር ከተማ)፣ ምህረት አየለ (ቦሌ ክፍለ ከተማ) ፣ ሊዲያ ኢያሱ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ) ፣ ሳውያ መሐመድ (ፋሲል ከነማ)፣ እመቤት ዘካሪያስ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ)፣ ኦጁሉ ኦዶንግ (ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ) እና ሲርያ ተሾመ (ጉለሌ ክፍለ ከተማ) በአጥቂ መስመር ጥሪ ቀርቦላቸዋል። ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም በካፍ የልህቀት ማዕከል በመሰባሰብ ዝግጅት ማድረግ እንደሚጀምሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዛምቢያ ጋር የመጨረሻ ዙር የማጣሪያ ጨዋታውን ሰኔ 27 እና ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ያደርጋል። 10ኛው የፊፋ የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ 24 ሀገራት ይሳተፋሉ። በዓለም ዋንጫው አፍሪካ ሞሮኮን ጨምሮ በአምስት ሀገራት ትወከላለች። ከሞሮኮ ውጪ በማጣሪያ የሚያልፉ አራት የአፍሪካ ሀገራት በመጨረሻ ዙር ጨዋታዎች ይለያሉ።
አካባቢ ጥበቃ
በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል
Jun 8, 2026 844
ባህር ዳር፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና የኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን የክልሉ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። ዓለም አካባቢ ቀን "የአየር ንብረት ለውጥ ተጽኖን መታደግ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። የባለስልጣኑ ዋና ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ በመድረኩ እንደገለጹት፣ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያገዘ ነው። የኮሪደር ልማትም ከተሞችን ጽዱ፣ ውብና አረንጓዴ በማድረግ የአካባቢ ጥበቃንና እንክብካቤ ሥራ እንዲፋጠን አስተዋጾ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል። ማንኛውም የልማት ፕሮጀክት ዘላቂነቱ የሚረጋገጠው ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በተጣጣመ መልኩ ሲተገበር መሆኑን ገልጸው፣ ይህም በክልሉ ተግባራዊ መደረጉን ጠቁመዋል። በክልሉ የልማት ሥራዎች ከአየር ንብረት ጋር ተጣጥመው እንዲከናወኑ መደረጉ እንደ ጎርፍ እና በረሀማነት ያሉ ችግሮችን ለመቀነስ መቻሉን ተናግረዋል። በአማራጭ የሃይል አቅርቦት ላይ የተመሰረተ ልማትም የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን አስረድተዋል። የአካባቢ ብክለትን ለመከላከልም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለህብረተሰቡ በዘመናዊ ቆሻሻ አወጋገድ ላይ ትምህርት በመስጠት ለውጥ እየታየ መምጣቱን ጠቁመዋል። ይህም ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በባለስልጣኑ የአየር ንብረት ለውጥ አካቶ ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አወቀ ይታይ የመወያያ ጽሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በግብርና፣ በትራንስፖርትና በከተማ ልማት ዘርፎች የአየር ንብረት ጉዳይን አካቶ እየተሰራ ነው። በማሳያነትም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና በኮሪደር ልማት ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።
በክልሉ በሚቀጥሉት የክረምት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለመኸር እርሻ አመች ነው
Jun 8, 2026 556
ጋምቤላ፤ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በሚቀጥሉት የክረምት ወራት የሚኖረው የዝናብ ስርጭት ለመኸር እርሻው አመች መሆኑን በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የጋምቤላ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ለ2018 ዓ.ም የክረምት ወቅት ያወጣው ትንበያ እንደሚያሳየው፣ በዘንድሮው መኸር የሚኖረው የዝናብ ስርጭት መደበኛና ለአዝመራው አመቺ እንደሚሆን ይጠበቃል። ይህ መረጃ ክልሉ ካለው ሰፊ የሩዝ፣ የበቆሎና የጥራጥሬ ሰብሎች ልማት አቅም አንጻር አርሶ አደሩና የኢንቨስትመንት አካላት አስቀድመው እንዲዘጋጁ ትልቅ እገዛ ያደርጋል። የጋምቤላ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋሁን ዓለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በሚቀጥሉት የክረምት ወራት የሚኖረው ዝናብ መደበኛና ብዙ ከመደበኛ ያላለፉ የዝናብ ስርጭት እንደሚሆን ይጠበቃል። በክልሉ የሚኖረው የዝናብ ስርጭት በአብዛኛው መደበኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለመኸር እርሻው መሳለጥ ዓይነተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በተለይም አርሶና ከፊል አርብቶ አደሩ የግብርና ልማቱን ለማከወንና ለመከታተል ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር መሪ ስራ አስፈፃሚው ገልጸዋል። በአንፃሩ የዝናቡ ዝርጭት በአብዛኛው መደበኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለወባ ትንኝ መራባት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ የወባ በሽታ ሊጨምር ስለሚችል አስፈላጊው ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል ብለዋል። እንዲሁም አልፎ-አልፎ በሚኖረው ከመደበኛ ያለፈ የዝናብ ስርጭት ቅጽበታዊ ጉርፍ ሊከሰት ስለሚችልም ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አቶ ተስፋሁን አስገንዝበዋል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው ተግባራዊ የተደረጉ ፕሮጀክቶች ለአካባቢ ጥበቃ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው
Jun 6, 2026 1445
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018(ኢዜአ)፦ የወንዝ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማቶችን ጨምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው የተተገበሩ ፕሮጀክቶች ለአካባቢ ጥበቃ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ገለጸ። የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ53ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ33ኛ ጊዜ ተከብሯል። ቀኑን ምክንያት በማድረግም ከፌዴራልና ከአዲስ አበባ ከተማ የተውጣጡ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የስራ ሀላፊዎች እና ባለሙያዎች ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ የተሰራውን የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ፕሮጀክቱ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቆ ክፍት መደረጉ ይታወሳል። የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተነድፈው የተተገበሩ ፕሮጀክቶች የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው። በአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰው፤ ይህም የአየር ብክለት መቀነስን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች እያስገኘ ነው ብለዋል። ይህም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲቸራት ያስቻለ መሆኑን በመጠቆም፤ ሥነ ምህዳርን በማሻሻል በኩል ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም አብራርተዋል። የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ፕሮጀክት አካባቢ ጥበቃን ውጤታማ እያደረጉ ካሉ ሥራዎች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመው፤ የእንጦጦ ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ለዚህ አይነተኛ ማሳያ ነው ብለዋል። በፕሮጀክቱ ሀገር በቀል ዛፎች መተከላቸውን ጠቅሰው፤ ሀገር በቀል የኮንሶ የአካባቢ ጥበቃ እውቀቶች አሻራ ያረፈበት መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም አንስተዋል። መሰል የአካባቢ ጥበቃና ልማት ሥራዎች ኢትዮጵያ ተምሳሌታዊና ተጠቃሽ ሀገር እያደረጋት ነው ሲሉም ዋና ዳይሬክተሯ አመላከተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ እሸቱ ለማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የእግረኛ መንገዶች፣የሳይክልና አማራጭ መንገዶችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም በተሽከርካሪዎች ወደ አየር የሚለቀቀውን በካይ ጋዝ እንዲቀንስ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል። ፕሮጀክቱ ከሕዝቡ ጋር በመሆን ለውጤት በቅቷል ከዚህ በኋላ ፕሮጀክቱ በሚጠበቀው ደረጃ አገልግሎት እንዲሰጥ ሕዝቡ ሊንከባከበው ይገባል ብለዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ዶኤ (ዶ/ር)፤ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያዊያን አቅም በአጭር ጊዜ ተገንብቶ ለውጤት መብቃቱ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ላይ ላላት ቁርጠኝነት መሰል የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ምስክሮች ናቸው ያሉት ተወካዩ ተፈጥሮን ከዘመናዊነት ጋር አጣጥሞ መሄድ ያለውን ውጤት አመላካች ነው ሲሉ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር ያስችላል
Jun 5, 2026 1509
አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ማጠናከር የሚያስችል መሆኑን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን እና መሠረተ-ልማት ዲቪዚዮን ዳይሬክተር ሮበርት ሊሲንጌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን በሚያሳልጡ በትራንስፖርት፣ ኢንዱስትሪ፣ ኃይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂዎች እና በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ በትኩረት እየሰራች ነው፡፡ በዚህም በየዓመቱ ለነዳጅ የሚወጣውን ወጪ መቀነስና በታዳሽ ኃይል የሚመራ የትራንስፖርት ሥርዓት መገንባት የሚያስችል ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂና የትግበራ ዕቅድ ይፋ አድርጋለች፡፡ በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የቴክኖሎጂ፣ኢኖቬሽን እና መሠረተ-ልማት ዲቪዚዮን ዳይሬክተር ሮበርት ሊሲንጌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፥ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂ ከዓለም አቀፍ የህግ ማዕቀፎች ጋር የተናበበ ነው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ የሚገባ ነዳጅ ጥገኛ በመሆናቸው ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጭ እንደሚዳረጉ ገልጸው፤ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ስትራቴጂና የትግበራ ዕቅድ ወጭን ከመቀነስ ባሻገር ለአስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ዋስትና ይሆናል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እያደረገች ያለችው ሽግግር የአየር ብክለትን በመቀነስ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት አጋዥ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር እስከ 2030 አዲስ ከሚመዘገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል 30 በመቶ የሚሆኑትን በሀገር ውስጥ ለማምረትና ለመገጣጠም ማቀዷ በአፍሪካውያን መካከል ያለውን የንግድ ትስስር ያጠናክራል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና መጀመር ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚደረገውን ሽግግር ያሳልጣል ያሉት ዳይሬክተሩ፥ በአህጉሪቱ ያለውን የንግድ እሴት ሰንሰለት እንደሚያቀላጥፍም ገልጸዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት አለብን-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
May 25, 2026 6012
አዲስ አበባ፤ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን አንድነት የበለጠ በማጎልበት የበለፀገች አህጉር መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 63ኛው የአፍሪካ ቀን ''የ63 ዓመታትን ዓመታት አንድነት፣ ትስስርና ልማት፤ አብረን እናክብር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል። በዝግጅቱም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማቶችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና በየ ጊዜው እየታደሰ መምጣቱን ገልጸዋል። የአህጉሪቷ የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ዕድገትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የአፍሪካን ጥቅል የሀገር ውስጥ ዕድገት ምጣኔ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያደርሰዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የአፍሪካ ወጣቶችም ሌሎች አህጉራት ጭምር የሚመኟቸው የአህጉሪቷ ዕድገትና ብልፅግና አቅም መሆናቸውን አንስተዋል። በቀጣይም የአፍሪካዊያንን የአንድነት ኃይል የበለጠ በማጎልበት የአህጉሪቱን ዕምቅ ፀጋዎች ለሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና መቀየር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ በበኩላቸው፥የአፍሪካዊያን ባህልና ዕሴት ለአህጉሪቷ መፃኢ ዕድል፣ ዕድገትና ብልፅግና የሚተርፍ የጥንካሬ ምንጭ ነው ብለዋል። የአፍሪካን የትብብር አቅም በማጎልበት የአህጉሪቷ ዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥና የራስን የተሻለ ዕድል መቅረፅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ለዚህም በሁሉም ዘርፍ የአፍሪካን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስፋት የአህጉሪቱን ዕምቅ የልማት ፀጋ ወደ ዘላቂ ብልፅግና መቀየር እንደሚገባ ተናግረዋል። በአህጉሪቷ ላይ የደረሱ በደሎች ፍትሕ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገርም ለአጀንዳ 2063 ስኬት በቁርጠኝነት በመስራት የወደፊት እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በየዓመቱ የአፍሪካ ቀን መከበር የጀመረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁን የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ1963 መመስረቱን እንደሆነ ይታወቃል። የዘንድሮው የአፍሪካ ቀንም የህብረቱ ኮሚሽን ከህብረቱ ሰራተኞች ማኅበር፣ አባል ሀገራት፣ ከህብረቱ አደረጃጀቶችና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር በመተባበር ተዘጋጅቷል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ ነው
May 13, 2026 5626
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሕብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰላም፣ በጸጥታ፣ በዘላቂ ልማት እና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ተቋማዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፈርመውታል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በዚሁ ወቅት በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪካ ህብረት ለታዳጊው ዓለም የፍትህ ድምፅ እና ለባለብዙ ወገን ግንኙነት ዋነኛ መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። አጋርነታቸውን ይበልጥ ተቋማዊ የሚያደርገው ይህ ስምምነት በቁልፍ ዘርፎች ላይ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የወደፊት ዕቅዶችን መነሻ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ በቋሚ አባልነት አለመካተቷን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ይህም የምክር ቤቱን ተቀባይነትና ውጤታማነት እንደሚጎዳው አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ሊስተካከል እንደሚገባ ጠቅሰው አፍሪካ ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወጥታ ለአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የማምረቻና የማጣሪያ ማዕከል መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ እና የተባበሩት መንግሥታት የ2030 አጀንዳ የተጣጣሙ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት ማሻሻያ ተደርጎ የአፍሪካ ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በናይሮቢ የተካሄደው የ"አፍሪካ ፎርዋርድ" (Africa Forward) ጉባኤ ውጤቶች ክትትል እንዲደረግባቸው አሳስበዋል፡፡ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብትን ጨምሮ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራት የሚለውን የአህጉሪቱን ጥያቄ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለውን ስልታዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል። 10ኛው የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ነው
May 13, 2026 4456
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረግ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያንጸባርቅ ተግባር መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት እየተካሄደ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስታቱ ድርጅት በሁሉም ዘርፎች ቀዳሚ ተግባር አፍሪካን የማድረግ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ግዴታ አለበት። አፍሪካ አህጉራዊ ግጭቶችን በማርገብ፣ አህጉራዊ ዕድገትና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናና ሌሎች የሰላምና ጸጥታ ኢኒሼቲቮች አስደናቂ መሆናቸውን ገልጸዋል። አፍሪካ በዓለም ሁለንተናዊ እንቅስቀሴ ላይ ያላት ሚና የጎላ መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ በታሪክና በዓለም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር የደረሰባትን በደል ለመቀልበስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ባልወጡበት ወቅት የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት አህጉሪቱ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዳይኖራት ማድረጋቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ ባልተሳተፈችበት የተቋቋሙ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኢ-ፍትሐዊነት አፍሪካን ብዙ አሳጥቷታል ያሉት ዋና ጸሀፊው፤ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካ ለመፍታት የተጀመሩ ኢንሼቲቮችን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት አፍሪካዊ ግጭቶች በአፍሪካ ማዕቀፍ እንዲፈቱ በመሪነት ከመሳተፍ ባለፈ የአፍሪካ ሕብረትን ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁመዋል። አፍሪካ በወሳኝ ማዕድናትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ አቅም እንዳላት ገልጸው፤ ሀብቷን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ የምታቀርብበትን መንገድ መቀየስ ይገባል ብለዋል።
አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም ለማቋቋም ወሰነች
May 13, 2026 4361
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ለ2030 እና አጀንዳ 2063 ግቦች የሚያስፈልጋትን የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የተዛባውን የዓለም የፋይናንስ ስርዓት የሚያጣጥም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (African Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 10ኛ ዓመታዊ ኮንፍረንስ በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ፣ ዘላቂ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደርና በተለዋዋጭ ዓለም የአፍሪካ ፈተናዎች ዙሪያ የሚያተኩር ነው። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ጨምሮ የዓለም ነባራዊ ሁኔታ በአሕጉሪቱ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋም የሚደረግ ጥረት ቢኖርም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሰቃዩበትና የሚሰደዱበት አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል። ይሄውም በአፍሪካ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ከጸጥታ ባለፈ በመልካም አስተዳደር፣ በልማትና የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት አስቻይ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል። በአፍሪካ የልማት ፋይናንስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር፤ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ አስተዳደር የአጀንዳ 2063 እና 2030 ግቦችን ለማሳካት እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል። በተለይም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተቋቋሙና አሁንም ያለው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ለአፍሪካ ፍላጎትና እውነታ ምላሽ የማይሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም አፍሪካን ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ጋር ለማጣጣም የራሷን የብድር ደረጃ መመጠኛ ተቋም (Africa Rating Agency) ለማቋቋም መወሰኗን ገልጸዋል። ይሄውም የአፍሪካ ሕብረት በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ሲሰራ ቆይቶ እ.አ.አ በመጪው ሰኔ ወር 2026 በሞሪሼስ በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በአፍሪካ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን ገልጸው፤ በብዙ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ንሯል፤ በአንዳንድ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ከ100 እስከ 150 በመቶ ጨምሯል ነው ያሉት። የአፍሪካ ሕብረት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ፣ የእርስ በርስ ትብብሩን ለማጠናከር በቅርበት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ሁለቱ ተቋማት አጋርነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው በመግለጽ፤ በተቋማቱ መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደፊት ማሻገር ያስፈልጋል ብለዋል።
ሐተታዎች
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 5253
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 24, 2026 5082
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የመደመር ማሳያ ከሳምንቱ አበይት ክስተቶች መካከል የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች በአሶሳ ከተማ ያስገነቡት የጋራ ሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህንፃ ምረቃ ይጠቀሳል። በክልሎቹ ትብብር የተከናወነው የህንፃ ግንባታ በመደመር እሳቤ የዜጎችን የጋራ ሰላም ለማስጠበቅና የልማት ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ ጥረት ማሳያ ነው። መርሃ ግብሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) የተገኙበት ነበር። በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም ላይ ያተኮረው መድረክ በሶማሌ ክልል ጂግጂጋ ከተማ የተካሄደውና በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ ያተኮረው ፎረምም በእዚህ ሳምንት ዐበይት ጉዳይ ነበር። ፎረሙ የተካሄደው “ቀጣናዊ ተቋማትን ማጠናከር ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሆን የተዘጋጀውም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በሰላም እና ፖለቲካዊ ምክክር ማዕከል (CRPP)፣ በሶማሌ ክልል መንግስት እና በሌሎች አጋር አካላት ነው። በፎረሙ መክፈቻ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ፣ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፤ መድረኩ የውጭ ተዋናዮች ሳይገቡበት የቀጣናው አካላት በራሳቸው ጉዳይ፣ ፖሊሲና እርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ብቻ የሚመክሩበት መሆኑን ጠቅሰዋል። እርስ በእርስ ለመተዋወቅ፣ ግልጽነትን ለመፍጠርና ጠንካራ ትስስርን ለመገንባት የሚያስችል በመሆኑም በቀጣናው ግጭቶች ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚረዳ ነው ያነሱት። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ምሁራን ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቀጣናው ፈተናዎች ተጨባጭ መፍትሄና አቅጣጫ እንዲያስቀምጡም ያግዛል ብለዋል። የጉባ ላይ ብስራቶች ተግባራዊ ልማት የሳምንቱ የበረራ ቅኝታችን የሚጀምረው ወደ ሶማሌ ክልል ጎዴ ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በስፍራው እየተገነባ ያለውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላም በምግብ ራስን የመቻል ጥረትን ለማሳካት የመሬት፣ ውሃ እና የሚያለማ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው በዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በቂ ሃብት ያላት መሆኑን ገልጸዋል። በምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህን ካሟላን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚተርፍ ነገር ማድረግ ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካን ጨምሮ የኒውክለር ሃይል ማመንጫ፣ የቢሾፍቱ አየር መንገድ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ፣ የነዳጅ ማጣሪያና የቤቶች ልማት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጓቸው የጉባ ብስራቶች መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካ መርቀው ስራ ያስጀምሩትም በዚሁ ሳምንት ነበር። በግራንዴር ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተገነባው ፋብሪካ፣ መሰረት ልማቱ በ300 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ፣ የዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የሴራሚክና የፎርሲሌን ንጣፎች ማምረቻ ፋብሪካ ነው። የፋብሪካው መገንባት የውጭ ምርት ጥገኝነት ከመቀነስ ባለፈ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት መሆኑ ታውቋል። የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ ጉብኝት በዚሁ ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ወደ ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመጓዝ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በድሬዳዋ ቆይታቸው ብርቱካንና ሌሎች የፍራፍሬ ልማት ሥራዎች እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ልማት ስራን ተመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጉራዋ ወረዳም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የግብርና ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባስተላለፉት መልእክትም የጋራ ሙለታ ተፈጥሯዊ የልማት ፀጋና ከፍታም ታሪክን፣ ውብ መልክዓ ተፈጥሮን የታደለ፣ የኢትዮጵያን ሜዳና ተራሮች ምርት የሚታፈስባቸው የማድረግ ሀገራዊ ጉዞ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ማሳያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ ተገኝተው 142 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶችን መርቀው ሥራ ያስጀመሩትም በዚህ ሳምንት ነበር። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር በለውጡ ዓመታት ከልማት የራቁ አካባቢዎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ብዙ መሰራቱን አንስተዋል። የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የንጽህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ፕሮጀክቶች ለዚሁ ማሳያ ናቸው ብለዋል። በተመሳሳይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ እና የመስኖ ፕሮጀክቶች መርቀው ለአገልግሎት አብቅተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በተለይ አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች ሲሄዱ ይደርስባቸው የነበረን እንግልት የሚያስቀር ነው። የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። በሲዳማ ክልልም በፌደራል መንግስት ድጋፍ በ460 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታም ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 75 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ነው። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከ543 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 52 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መመረቃቸው ሌላው የሳምንቱ ክስተት ነበር። በዞኑ ለምረቃ ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤና፣ የውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትንም መርቀዋል። ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ የሚደረግበት የሃዋሳ ከተማ ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም በዚህ ሳምንት ተካሂዳል። ለፕሮጀክቱ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ የፕሮጀክቱ ግንበታ ሲጠናቀቀ ሀዋሳ ከተማዋን ጽዱ በማድረግ የቱሪዝምና የኢንቨስመንት ማዕከልነቷን ያሳድገዋል ተብሏል። አቶ ደስታ የፕሮጀክቱ ግንባታ መንግስት ለከተሞች እድገት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉም ነው የጠቀሱት። የከሰም መስኖ ግድብ የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክትም በዚሁ ሳምንት ተመርቆ ሥራ ጀመሯል። ፕሮጀክቱ የተመረቀው በአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ነው። የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ያስቀራል ተብሏል። በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብርሃም (ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር። የጥገና ማሻሻያው በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን ይህን የአደጋ ስጋት በማስቀረት ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል የሚያስችል ነው። ለፕሮጀክቱም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ሚኒስትሩ አንስተዋል። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፤ ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል። የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የሀዝቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም አንስተዋል። የግንቦት - ታላቁ ሁነት ከ50 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ድምጻቸውን ለመስጠት የተመዘገቡበት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ሂደቱን ስኬታማ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አጠቃላይ ዜጎችና የሚመለከታቸው ሁሉ ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በዚሁ ሳምንት "ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት የመገናኛ ብዙሃን ሚ ና" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአዳማ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፤ የዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት የዜጎች ጠንካራ ተሳትፎና የዳበረ የዴሞክራሲ ልምምድ የታየበት መሆኑን አንስተዋል። ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅም መገናኛ ብዙሃን የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል። ከተረጅነት የመውጣት ሀገራዊ ጥረት በድሬዳዋ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የውይይት መድረክም ሌላው የእዚህ ሳምንት ዓቢይ ጉዳይ ነው። መድረኩን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የግብርና ሚኒስቴር በመተባበር ያዘጋጁት ነው። በመድረኩም በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተነስቷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በምግብ ራሱን የቻለ ትውልድ የመገንባት ጥረት የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት እውን የማድረግ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቂና የተሟላ የውሃ ሀብት፣ የተማረና አምራች የሆነ ወጣት የሰው ኃይል እንዲሁም ለም የመሬት ፀጋዎች ያሉባት ሀገር በመሆኗ በማልማት እድገትና ማንሳራራትን ማስቀጠል ይቻላል ሲሉ ተናግረዋል። ለእዚህም ዋናው መሠረታዊ ጉዳይም ያሉ አቅሞችን በመለየትና ህዝብን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ በማሸጋገር በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጡን ሥራ በላቀ ደረጃ ማስቀጠል መቻል መሆኑን አንስተዋል። ለሰላም ጥሪ የተሰጠ ምላሽ የሠላም ጥሪን የተቀበሉ የአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመረከብ፣ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግና የመልሶ ማቋቋም (ዲዲአር) መርሀግብርም በዚህ ሳምንት ተከናውኗል። በብሔራዊ ተሀድሶ ማዕከል ጠዳ ጊዜያዊ ማሰልጠኛ ማዕከል በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ የቀድሞ ታጣቂዎች ከስልጠና በኋላ ከምንም በላይ የሰላም ዘብ ሆነው የበደሉትን ህዝብ ለመካስ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ታጣቂዎቹ ሠላምን አማራጭ በማድረግና የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለሠላም ያደረጉት አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል። የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፣ መንግስት ለሠላም ባለው ጽኑ አቋምና ፍላጎት የሠላም ጥሪውን ተቀብለው የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ እያደረገ ነው ብለዋል። በተመሳሳይ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የክልሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በኮምቦልቻ የስልጠና ማዕከል ስልጠና የጀመሩ መሆኑ ይታወቃል። ሐረር- ፕሮጀክቶች ምረቃ የሐረሪ ክለል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙትን የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ሌሎች የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝትም ሌላው የእዚህ ሳምንት ኩነት ነበር። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተሻለ አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ። በተለይም የሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መገንባት የክልሉን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የበለጠ በማሳደግ ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ነው ያነሱት። በዘመናዊ ትምህርት የታነፀና በእውቀት የበለፀገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማፍራት ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቶቹ በፍጥነትና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ለማስቻል በአስተዳደሩ በኩል ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት 672 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በይፋ የተመረቀውም በዚህ ሳምንት ነው። በምረቃው ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን፣ የክልሉ የመንገዶች ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢድሪስ ሙሴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እንደገለጹት ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የከተማውን የንግድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያስችል ነው። የከተማውን ገፅታ በመለወጥ ረገድም የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ነው ያነሱት። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገድ ፕሮጀክቱ የጂግጂጋ ከተማን ልማትና ዕድገት በማፋጠን በኩል ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የመንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ አብዱራህማን አስተዳደሩ ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ዕቅድን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጂግጂጋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 30 ሜትር ስፋት እንዳለውም ታውቋል።
የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር
May 17, 2026 4672
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018 (ኢዜአ)፦ የክልሎች ቅኝት- በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን። 👉የግንቦት - ታላቁ ሁነት የምርጫ ጉዳይ ወቅታዊና ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ በሁሉም አካባቢዎች የዜጎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለበት ሳምንት ነው። መራጮች ካርዳችንን ለሀገርና ለህዝብ ይበጃል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በተመቻቸላቸው ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ ዓምድ የፖሊሲ አማራጮቻቸውንና ማኒፌስቷቸውን እያስተዋወቁ ቀጥለዋል። የተለያዩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዜጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። ለዘንደሮው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሰማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። 👉የመጠጥ ውሃ ችግሮችን የመፍታት ጥረት ማሳያዎች በሳምንቱ በወላይታ ዞን ከ150 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ ወረዳ ብዝሃ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል። ፕሮጀክቶቹን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) መርቀዋል። የፕሮጀክቶቹ ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የላቀ ትርጉም እንዳለው ተነስቷል። በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሀመድ በቀብሪደሃር ከተማ በ407 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄድ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀምረዋል። ከለውጡ በኋላ በክልሉ ከ370 በላይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓዶች ተቆፍረው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። በዚህም የመጠጥ ውሃ ሽፋኑ ከ19 ወደ 52 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ታውቋል። በምስራቅ ሐረርጌ ዞንም የደደር ከተማንና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት ታስቦ የተገነባው ፕሮጀክትም ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው በዚሁ ሳምንት ነበር። የፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ሃላፊ መሰረት አሰፋ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር እና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ደደር ከተማን ጨምሮ ሌሎች በወረዳው ሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል። 👉የጤና ጉዳይ የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ የህክምና እና የምርመራ ዘመቻ ከግንቦት 3 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በስምንት ክልሎች በሚገኙ 154 ወረዳዎች የሚያካሄድ መሆኑ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ይሄው መርሃ ግብር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩ በተለይም ትምህርት ቤቶችን ማዕከል በማድረግ የሚከናወን ሲሆን ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል አላማ ያደረገ መሆኑም ተገልጿል። 👉ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የተካሄደው የውይይት መድረክም የሳምንቱ አበይት ጉዳይ ነበር። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና ልማት በተለይም የስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ አልፎ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተመዘገበውን የላቀ ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል። በሌሎች የተለያዩ የግብርና የልማት ስራዎችንም በተጠናከረ መልኩ በማከናወን ምርታማነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ መቀየር ይኖርብናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሠይፈ ደርቤ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረው ግብ እንዲሳካ በቂ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ለዚህም ሚዲያ የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸው ኢዜአ ይህንን ሀገራዊ ትልም ለማሳካት የይዘት ስራዎችን በስፋት ተደራሽ የማድረግ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 👉የምግብ ስርዓት ሽግግር በጋምቤላ ክልል ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የምግብ ስርዓት ሽግግር እና የኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጋምቤላ ከተማ በይፋ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)፤ በክልሉ የተሟላ ስርዓተ ምግብን በማረጋገጥ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል። 👉ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በአሶሳ በአሶሳ ከተማ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የተጀመረው በዚሁ ሳምንት ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ የትምህርት ቤቱን ግንባታ አስጀምረዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 34 ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ መሆኑን ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ትምህርት ቤትም በአንድ ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ብለዋል። 👉የሰላምና አብሮነት እሴት ግንባታ የሐረሪ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና የማያ ከተማ አስተዳደር "የህዝቦች ሰላምና አብሮነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ የህዝብ ለህዝብ የሰላምና አብሮነት ኮንፍረንስ የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ የሐረርጌ ህዝቦች ትስስር በሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጠውና ለታላቅ ማህበራዊ ውህደት ተምሳሌት እንደሚሆን ገልጸዋል። የኮንፈረንሱም ዓላማ የሰላም እሴት ግንባታና የልማት ትስስርን ይበልጥ ማጠናከር ስለመሆኑ አንስተዋል። 👉የግብርና ልማትና ምርታማነት በአማራ ክልል ለዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማዘጋጀት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ያስታወቀው በዚሁ ሳምንት ነው። የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱ ታውቋል። 👉በኦሮሚያ ክልልም ለዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካል የሆነው ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን፤ በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አቮካዶን ጨምሮ አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ስለመዘጋጀታቸውም ተናግረዋል። በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል። 👉የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የበቆሎ ማሳ በመስክ የተመለከቱትም በዚሁ ሳምንት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተደረጉ ባሉ ጥረቶች ውጤት እየተገኘ ነው። በዚህም በበልግ ወቅትም ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብአቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል። በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል። 👉የኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው የመረቋቸው የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ሥራ የጀመሩትም በዚሁ ሳምንት ነው። የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ፤ በኮምቦልቻ የኢንዱስትሪ ልማት ይበልጥ እያንሰራራ ስለመሆኑ አንስተዋል። በኢንዱስትሪ ከተማዋ ኮምቦልቻ በድምሩ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን ገልጸው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረትና ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትን በመተካት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ እየሆኑ ነው ብለዋል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 10, 2026 4899
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 2/2018 (ኢዜአ)፡- በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር በመቃኘት ማስታወስ ይሆናል። በመሆኑም በዚህ ሳምንት በሀገራችን ሁሉም ክልሎች ምን ምን ዋና ዋና ጉዳዮች ነበሩ ስንል እንጠይቃለን? የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምልከታ- በሱሉልታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳምንቱ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ በ2 ሺህ 150 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ጎብኝተዋል። መንግሥት በግብርናው ዘርፍ በወሰዳቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች እየተገኙ ያሉ ውጤቶች አመርቂና ለቀጣይ ሥራዎች ስንቅ መሆናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ተናግረዋል። መሬት ጦም ማደር የለበትም በሚል ጽኑ እምነት የተጀመረው የበጋ ስንዴ ልማት አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ስለመሆኑም አንስተዋል። ከልመና ራሳችንን መገላገል አለብን፤ ሊታረስና ሊለማ የሚችል መሬት መታረስ አለበት በሚል ጽኑ እምነት የበጋ ስንዴ ልማት መጀመሩን አስታውሰው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አሁን ላይ አስደማሚ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል። የቱሪዝም ልማት የወፍ በረር ጉዟችን የቀጠለ ሲሆን ከሱሉልታ ቀጥታ ወደ አማራ ክልል ባህር ዳር አምርተናል። የባህር ዳር መዳረሻችን በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ይሆናል። የሪዞርቱ ግንባታ ተጠናቆ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ ባሳምንቱ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" እቅድ መሰረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት አላማ በማድረግ ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መገንባቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ከተማ ቆይታቸው በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታም አስጀምረዋል። በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴልም በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የሚጠናቀቅ መሆኑ ታውቋል። የመልካ ቁንጡሬ ሁነት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀንን በዩኔስኮ በተመዘገበው በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ በሳምንቱ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል። የአፍሪካ ዓለም አቀፍ የቅርስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ10ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመልካ ቁንጡሬ–ባልጩት አርኪዮሎጂና ፓሊዮንቶሎጂ መካነ ቅርስ ስፍራ ተከብሯል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ህይወት ኃይሉ፤ ባህላዊና የተፈጥሮ ቅርሶች ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል። ሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ለህዝብ ይፋ የተደረገውም በዚሁ ሳምንት ነው። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው። የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን¸፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኩነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እየሆነች እንድትመጣ አድርገዋታል ብለዋል። የሀይቅ ዳርቻ ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ ብለዋል። የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። ጅማ ዞን ጎማ ሁለት በጅማ አጠር ያለ ቆይታችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጅማ ዞን ጎማ ሁለት የምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መቅረባቸውን በማስተዋወቅ የቅስቀሳ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የቅስቀሳ ስነ ስርአት ላይ የፓርቲው አባላትና አመራሮች እንዲሁም ደጋፊዎች በመውጣት የተሳተፉበት መሆኑን ለማየት ችለናል። በመርሃ ግብሩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ፤ በፓርቲው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው በመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተመሳሳይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ርዕሰ መስተዳድሩ በሚወዳደሩበት ምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳና እጩ የማስተዋወቅ መርሐ ግብር የተካሄደውም በዚሁ ሳምንት ነበር። ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት ብልፅግና ፓርቲ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንን ሲያከናውን ቆይቷል። በባለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገርን እድገትና የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን በመተግበር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል። የሽንሌ እመርታ በሳምንቱ በሶማሌ ክልል ሽንሌ ወረዳ የተገነባው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድና በሽንሌ ጠቅላላ ሆስፒታል የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻ ፋብሪካ በክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተመርቋል። በሽንሌ ወረዳ የመርማርሳ ከተማን ከድሬዳዋ ጋር የሚያስተሳስር የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታንም አስጀምረዋል። የተገነቡት የልማት ስራዎች በተለይም ለወረዳው እመርታ መሆኑን የገለጹት አመራሮቹ በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት የማልማትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ይቀጥላሉ ብለዋል። ሳተላይት በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀቢያ ጣቢያ ተከላ ስራ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በተገኙበት በዚሁ ሳምንት ተጀምሯል። የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ ሲሆን የመረጃ ግብዓት ከመሆን አኳያም ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል። የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ሌሎችም የተሟላ መረጃ ለመስጠት የሚጠቅም መሆኑ ታውቋል።
ትንታኔዎች
ባሳለፍነው ሳምንት …
Jun 7, 2026 1682
ባሳለፍነው ሳምንት … ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ባሳለፍነው ሳምንት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተካሂዷል። ድምፅ ለመስጠት 54 ሚሊየን 57 ሺህ 861 መራጮች መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማሳወቁ ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለመራጮች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምርጫው ወቅት ድምጽ ስለሰጡ መራጮች ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ መሆኑን ገልጸዋል። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል ብለዋል። ማገልገል መታደል መሆኑን ገልጸው፤ ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይህንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ ሲሉም አስገንዝበዋል። ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ሥራ አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 22 ነጥብ 25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን ይሸፍናል። ይህ ፕሮጀክት የማይቆራረጥ የልማት ሥራችን ኅያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሀገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው ሲሉም አስገንዝበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና 73 አባላት ከያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ጋር መክረዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ለዲሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎትና አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን ብለዋል። ዲሞክራሲያዊ ሂደቶች ከአኅጉራችን ነባራዊ ሁኔታና ተሞክሮ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ አፍሪካዊ ተቋማት ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የምርጫ ሂደታችንን ለመደገፍ በመላው ሀገሪቱ ታዛቢዎችን በማሰማራት የምርጫ ታዛቢ ልዑኩ ላደረገው ያልተቆጠበ ጥረት እውቅና እና አድናቆት እየሰጠን፤ የምልከታውን የተሟላ ውጤት እንጠብቃለን ሲሉም አመላክተዋል። የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻ ልማት፤ የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳን የያዘ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ባለው መስመር የሚከናወነው መጠነ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽንም፤ ከወንዞቹ ባሻገር እስከ 50 ሜትር የሚዘልቅ መሆኑን አስረድተዋል። የአረንጓዴ ኮሪደሮችን፣ የሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን እና የንግድ ቦታዎችን ልማት ማካተቱን ጠቅሰው፤ ከተማዋን በእጅጉ የቀየረ ነው ብለዋል። የወንዝ ዳርቻዎችን ገጽታ እና አገልግሎት ከማሻሻል ባለፈ በኮንስትራክሽን፣ በኢንጂነሪንግ፣ በመልክዓ-ምድር ውበት ግንባታ፣ በሎጂስቲክስ እና በተያያዙ ዘርፎች ለብዙ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም አብራርተዋል። አብዛኛው ሥራ በሀገር ውስጥ መሐንዲሶች መቀረጹና መተግበሩ፤ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በከተማ ልማት እና በመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸው ዐቅም እያደገ መምጣቱን ያሳያል ነው ያሉት። ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎች እና ቆሻሻዎች የሚጣሉባቸው፣ በወንዝ ዳርቻዎች በሚኖሩ ማኅበረሰቦች ላይ የጎርፍ አደጋ ይጋርጡ የነበሩት እነዚህ አካባቢዎች፤ አሁን ላይ ወደ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ለሕይወት ምቹ ወደሆነ የከተማ ቦታነት እየተቀየሩ መሆኑንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ ሁኔታም፤ የንግድ እና የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ተቀናጅተው መገንባታቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ከዚህ ቀደም ከነበረው ያልተናበበ ሥራ ተላቀው በጥናትና በጋራ ግብ ተባብሮ መሥራት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ስለመሆኑ አመላክተዋል። ይህ ፈጣን የልማት ሥራ አዲስ አበባን አረንጓዴ፣ ይበልጥ የተሳሰረች፣ በኢኮኖሚ ንቁ እና ሰውን ማዕከል ያደረገች ከተማ የማድረግ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ላይ መሰረት የተጣለበት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። #ባሳለፍነው_ሳምንት #ኢዜአ
በዓለም ላይ አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ …
Jun 3, 2026 2511
በዮሐንስ ደርበው በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር ሞላወርቅ አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በዓለምም ሆነ በሀገራችን አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው የደም ግፊት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በቆይታቸውም፤ ለደም ግፊት አጋላጭ ስለሆኑ ምክንያቶችና ሊደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄም እንዲሁም ከመድሃኒት አወሳሰድ ጋር በተያያዘ ሳይንሳዊ ማብራሪያዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን አቅርበዋል። · የደም ግፊት ምንድን ነው? ደም በደም ሥሮቻችን ሲያልፍ፤ የሚለካው መጠን “የደም ግፊት” እንደሚባል ዶክተር ሞላወርቅ ያስረዳሉ። የላይኛው (ሲስቶሊክ ወይም ከፍተኛው) የደም ግፊት መጠን ልብ በምትኮማተርበት ጊዜ ደም ወደ ደም ሥር ሲረጭ የሚለካው መሆኑንም ይገልጻሉ። የታችኛው (ዲያስቶሊክ ወይም ዝቅተኛው) የደም ግፊት መጠን ደግሞ ልብ ደም ለመቀበል ለአፍታ ዕረፍት በምታገኝበት ጊዜ የሚከሰት የግፊት ደረጃ መሆኑንም ይገልጻሉ። · የደም ግፊት ደረጃዎች እና ማስጠንቀቂያቸው ዶክተር ሞላወርቅ እንደሚሉት፤ የጤናማ ሰው የደም የግፊት መጠን 120 በ 80 እና በታች መሆን ይኖርበታል። በሌላ በኩል ግን ይላሉ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 የታችኛው ደግሞ ከ80 በታች ከሆነ “ከፍ ያለ ወይም የጨመረ የደም ግፊት ደረጃ” ይባላል። የላይኛው ከ130 እስከ 139 ወይም የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከሆነ ደግሞ “ደረጃ አንድ የደም ግፊት” እንደሚባል ያስረዳሉ። የላይኛው ከ140 በላይ ሲሆን እና የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ ደግሞ “ደረጃ ሁለት የደም ግፊት” እንደሚባል ነው የሚገልጹት። በሌላ በኩል “የከፋ የደም ግፊት ደረጃ” የሚባል እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም የላይኛው ከ180 በላይ እና የታችኛው ከ120 በላይ ሲሆን ነው በማለት ያብራራሉ። · ለደም ግፊት መጨመር መንስዔዎቹ ምንድን ናቸው? በዋናነት ሁለት ዓይነት የደም ግፊት መኖሩን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ ከፍተኛ የደም ግፊት እና መንስዔው የሚታወቅ የደም ግፊት መሆኑን አስረድተዋል። በዋናነት ወይም በአብዛኛው ከ90 እስከ 95 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ ደም ግፊት የሚባለው መሆኑን ገልጸው፤ በርካታ መንስዔዎች ሊኖሩት እንደሚችሉ ቢገመትም ሁሉም በውል እንደማይታወቁ ያነሳሉ። ከበርካታ መንስዔዎቹ መካከልም፤ በቤተሰብ የሚወረስ (ተላላፊ)፣ አካባቢያዊ ምክንያቶች እንዲሁም የአኗኗር ዘይቤ የሚሉት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል። የአኗኗር ዘይቤ ሲባልም፤ የአመጋገብ ሥርዓት በተለይም ጨው የበዛበት ምግብ፣ ክብደት መጨመር፣ አካባቢያዊ ሁኔታዎች (አልኮል መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ)፣ የስኳር ታማሚ መሆን የሚሉት ይጠቀሳሉ ይላሉ። · ለደም ግፊት በተለይም እነማን ተጋላጭ ናቸው? ዕድሜ በጨመረ ቁጥር የደም ግፊት የመከሰት ዕድሉም እንደሚጨምር ጠቅሰው፤ በዚህም መሠረት ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ተጋላጭ መሆናቸውን ይናገራሉ። እንዲም በቤተሰብ የደም ግፊት ኬዝ ያለባቸው ሰዎች፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒክ ግሩፕ) ለምሳሌ፡- በጥቁሮች (አፍሪካውያን)፣ በኤስያውያን፣ በደቡብ ኤስያውያን ላይ ከፍተኛ የደም ግፊት ሊከሰት እንደሚችል ይገልጻሉ። እንደ ዶክተር ሞላወርቅ ማብራሪያ፤ በአጠቃላይ አጋላጭ ምክንያቶች በሁለት ተከፍለው ሊታዩ ይችላሉ። አንደኛው፡- ልንከላከላቸው (ልንቀንሳቸው) የምንችላቸው መሆናቸውን በመግለጽ ይህም የአመጋገብ ሥርዓትን ማስተካከል፣ ክብደት መቀነስ፣ አልኮልና ሲጋራ ማቆም እና መሰል መሆናቸውን አብራርተዋል። ሁለተኛው፡- ልንከላከላቸው የማንችላቸው መሆናቸውን ገልጸው ይህም፤ የዕድሜ መጨመር፣ የማንነት ሁኔታ (ኢትኒሲቲ) እና በቤተሰብ የሚተላለፍ የሚሉትን ጠቅሰዋል። · የደም ግፊትን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? የደም ግፊ ከተከሰተ መቆጣጠር እንጅ ማዳን እንደማይቻል ገልጸው፤ ከላይ እንደተጠቀሰው አስቀድሞ መከላከል ወይም ማዘግየት የሚቻል እና መከላከል የማይቻል የደም ግፊት ደረጃ መኖሩን አስረድተዋል። · የደም ግፊት በውል የሚታወቅ ምልክት አለው? የደም ግፊት ሲከሰት ምልክት እንደሌለው በማንሳት፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ “ዝምተኛው ገዳይ” እስከመባል መድረሱን ዶክተር ሞላወርቅ ያነሳሉ። ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ግን፤ በአንድ ወይም በሁለት የሰውነት አካል ላይ ችግር ሊደርስ እንደሚችል ከዚህም ሲያልፍ እስከ ሞት እንደሚያደርስ ይጠቅሳሉ። በተያያዘም፤ የራስ ምታት፣ የዐይን ብዥ ብዥ ማለት፣ ትንፋሽ ማጠር፣ የድካም ስሜት፣ አንገት የመያዝ ዓይነት ስሜቶች የደም ግፊቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ሊስተዋሉ የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል። አክለውም፤ በአብዛኛው በሕብረተሰቡ ላይ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከፍተኛ ደረጃ ይደርስና ድንገት በጨመረ ጊዜ፤ ለሞት፣ ለአደጋ፣ ለልብ ድካም፣ አጣዳፊ ለሆነ የልብ ህመም፣ በጭንቅላት ላይ የደም መፍሰስ፣ የኩላሊት ድክመት፣ በደም ሥሮች በአግባቡ ደም እንዳይተላለፍ ማድረግ፣ ለዐይነ ስውርነት መዳረግን ጨምሮ መሰል ጉዳቶችን ሊያስከትል እንደሚችል አስገንዝበዋል። · መድኃኒት አወሳሰድ ላይ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ ዶክተር ሞላወርቅ እንደገለጹት፤ አንድ ሰው ደም ግፊት እንዳለበት ከተነገረው በኋላ ሕክምናውም እንደ ደም ግፊቱ ደረጃ ይለያያል። ይህንም በምሳሌ ሲያስረዱ፤ የላይኛው ከ120 እስከ 129 ከሆነ “የጨመረ ግፊት” ይባላል፤ እዚህ ላይ ሰውየው ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ አመጋገቡን እንዲያስተካክል፣ ስፖርት እንዲሠራ፣ ክብደት እንዲቀንስ፣ ሱስ (ሲጋራ፣ አልኮል) እንዲቀንስ ክትትል ይደረጋል ብለዋል። ስለዚህ መድኃኒት ሳይጀምር የአኗኗር ዘይቤን በማስተካከል የደም ግፊቱን ሊቀንሰው (ሊቆጣጠረው) ይችላል ማለት ነው ሲሉም ይገልጻሉ። “ደረጃ አንድ ግፊት” የሚለው ላይ ከደረሱ ግን ሕክምና የሚጀምሩም የማይጀምሩም እንዳሉ ተናግረዋል። ይህም ማለት የላይኛው ከ130 እስከ 139 የታችኛው ከ80 እስከ 90 ከደረሰ ሕክምና የሚጀምሩት የስኳር ህመም ያለባቸው፣ የስትሮክ ህመም ያለባቸው፣ ከልብና ደም ሥር የተገናኙ ህመሞች ያሉባቸው ከሆኑ ቢያንስ አንድ የግፊት መድኃኒት መጀመርና ክትትል ማድረግ አለባቸው ይላሉ። በሌላ በኩል ግን ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ ሰዎች “ደረጃ ሁለት ግፊት” ላይ ከደረሱ (የላይኛው ከ140 የታችኛው ከ90 በላይ ከሆነ) ሁሉም መድኃኒት መጀመር እንዳለባቸው በአጽንዖት ገልጸዋል። የሚጀምሩት መድኃኒትም አሁን ባለው በተሻሻለው የሕክምና ዘይቤ ሁለት መድኃኒቶች የሚጀምሩበት ሁኔታ እንዳለ ነው የሚያስረዱት። የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል ግን ለሁሉም የግፊት ዓይነቶች መሠረት (የሚመከር) መሆኑን አስገንዝበዋል። ስለዚህ መድኃኒት ጀምሬያለሁ ብሎ የአኗኗር ዘይቤው ላይ ቸልተኝነት ሊኖር እንደማይገባም ነው የሚመከሩት። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከግፊት ጋር በተያያዘ ወደ ሆስፒታል መጥተው የሚታከሙ ታካሚዎች አብዛኞቹ፤ ጀምረው ያቋረጡ፣ ለመጀመር ፍላጎት የሌላቸው፣ ቅድመ ምርመራ ባለማድረግ ምክንያት ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ የተጎዱ ናቸው ሲሉ አብራርተዋል። ስለዚህ የግፊት መድኃኒት ከተጀመረ ሊቋረጥ እንደማይችል አስጠንቅቀዋል። በየጊዜው ክትትል ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም አክለዋል። በሂደት እንደ ግፊቱ ሁኔታ መድኃኒቶች ሊቀነሱም ሊጨመሩም እንደሚችሉ አመላክተዋል። · የመስፋፋት ደረጃ የዓለም ጤና ድርጅት በ2024 ያወጣውን መረጃ ዋቢ አድርገው፤ 1/3ኛው የዓለም ሕዝቦች በደም ግፊት እንደሚጠቁ ዶክተር ሞላወርቅ አንስተዋል። ከእነዚህ መካከልም፤ 7 ነጥብ 6 ሚሊየን ገደማው በአንድም በሌላም ምክንያት ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ጠቁመዋል። አብዛኞቹ የደም ግፊት ታማሚዎች ቁጥር የሚመዘገበው ደግሞ በመካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ሀገራችንን ያካትታል ሲሉ ገልጸዋል። በሀገራችን ደረጃም ይላሉ ዶክተር ሞላወርቅ፤ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ባይኖሩም ከግፊት ጋር በተያያዘ በ2001 ላይ በ35 ሳይቶች የተጠኑ ጥናቶች ውጤቶች እንደሚያመላክቱት ከ21 እስከ 25 በመቶ ያህሉ ሕዝብ በደም ግፊት የሚጠቃ ነው ይላሉ። በአብዛኛው ደግሞ ከተማ ላይ እንደሚበዛ ጠቁመው፤ በተለይም አዲስ አበባ ላይ እስከ 30 በመቶ እንደሚደርስ የጥናቶቹ ውጤቶች ማመላከታቸውን ተናግረዋል። አብዛኞቹ ኬዞች ደግሞ ዕድሜያቸው ከፍ ያለ፣ ክብደታቸው የጨመረ፣ አልኮል እና ሲጋራ የሚጠቀሙ እና የስኳር ህመም ያለባቸው ሰዎች ጋር የሚገናኙ መሆናቸውን አስረድተዋል። እንደ ዓለም አቀፍ ደረጃም ኬዙ ካለባቸው መካከል ግማሽ ያህሉ ግፊት እንዳለባቸው እንኳን እንደማያውቁ ነው የሚገልጹት። ለግፊት ሕክምና ትክክለኛ ክትትል አድርገው ግፊታቸውን በአግባቡ የሚቆጣጠሩት ከ 5 ሰዎች 1 መሆኑንም ጥናቶች ያሳያሉ ብለዋል። · ምክረ ሐሳብ በሀገራችን በሕብረተሰቡ ዘንድ ለደም ግፊት መለካት ኬዙ ከተገኘም የሕክምና ክትትል የማድረግ ሁኔታዎች ዝቅተኛ መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ሕብረተሰቡ የደም ግፊት ምልክት ሳያሳይ ከአካል ጉዳት እስከ ሞት ሊያደርስ እንደሚችል ተገንዝቦ፤ የደም ግፊቱን የመለካት ልምምዱን ሊያዳብር እንደሚገባ ዶክተር ሞላወርቅ መክረዋል። በሌላ በኩል እንደ ሀገራችን ባሉ ሆስፒታሎች በጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ ወይም መቋረጥ (ስትሮክ) ካለባቸው ሰዎች ከ70 እስከ 85 በመቶው ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ የሚከሰት መሆኑን ገልጸው፤ ድንገተኛ ግፊት መጨመር ከልብ እና ከደም ሥሮች ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ጉዳት እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዓለምም ሆነ እንደ ሀገር አሳሳቢ ደረጃ ከደረሱ የህመም ዓይነቶች አንደኛው ግፊት መሆኑንም አረጋግጠዋል። ስለዚህ የደም ግፊትን መለካት፣ የአኗኗር ዘይቤን ማስተካከል፣ ከሱስ መራቅ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር ለጤናማ ሕይወት ከፍተኛ ሚና እንዳለው መክረዋል።
ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት
May 24, 2026 5641
በኢዜአ ዐይን ...! በዮሐንስ ደርበው ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ የመገንባት ሂደት እና የኮሪደር ልማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ጥቅምት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተገኙ ጊዜ፤ የኮሪደር ልማት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት መሆኑን ገልጸዋል። ከተማ ሲለማ ደግሞ ለነዋሪም ሆነ ለጎብኝ፤ ለዐይንም፣ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ውበትና ምቾት ማላበሱ አይካድም። የኮሪደር ልማት ጽዱ ከተሞችን ይሠራል፤ከትራንስፖርት፣ ከትራፊክ ምልክቶች፣ ከብስክሌትና እግረኛ መንገድ ደኅንነት ጋርም ተጣጥሞ ተሠርቷል። በዚህ ዐውድ የኮሪደር ልማት ውበትም ምቾትም ነው። መሠረተ-ልማት ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ እንዲጠቅምም የኮሪደር ልማት ሚና የላቀ ነው። እንግልትንና ብልሹ አሠራርን መቅረፊያ ብልኀት - መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለአንጀት ካንሰር አጋላጭ ምክንያቶች በውል ይታወቃሉ? ቀድሞስ መከላከል ይቻላል? የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን ኢትዮጵያ በከተሞቿ እና ገጠራማ አካባቢዎቿ የኮሪደር ልማት እያከናወነች ነው። ይህ በኢትዮጵያ ከውበት በላይ ነው። ለምን ቢሉ? ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ስላለው ይሆናል መልሱ። · ማኅበራዊ መሥተጋብርን በመጠገን፡- ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁባቸው አንዱ በየዐውዱ የሚገለጠው ጥብቅ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸው ነው። በጋራ መንቀሳቀስ፣ መጫዎት፣ ከቤት ወጣ ብለው መመካከር የኑሯቸው አካል ነው። ይሁንእንጅ በተለይም ከተሜው ከወዳጅ ጋር በኅብረት በእግር ወይም በብስክሌት ለመንቀሳቀስ፣ አረፍ ብሎ የሚያወጋበት በቂ አረንጓዴ ስፍራና ፓርኮች ባለመኖራቸው ማኅበራዊ መሥተጋብሩ እየላላ የመጣ ይመስላል። አሁን የኮሪደር ልማት በደረሰባቸው ከተሞች፤ሰዎች ሲያሻቸው በእግር አሊያም በብስክሌት ከወዳጆቻቸው ጋር የልባቸውን እያወጉ ለመንቀሳቀስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሰዎች በእንቅስቃሴያቸው መሐል ዐረፍ ማለት ቢሹም ችግር የለም፤ አሁን እንደ ድሮ አይደለምና። አረንጓዴ መናፈሻ ስፍራ ፍለጋ ከከተማ መውጣት አያሻም። በሌላ በኩል ወጣቶች እና ሕጻናት ኳስ የሚጫወቱበት ስፍራ መመቻቸቱ ጤናን ከመጠበቅ ባሻገር፤ ማኅበራዊ መሥተጋብራቸውን ያጠናክራል። · ጤናማ አከባቢን በመፍጠር፡- የኮሪደር ልማት ለሰው ልጆች ከቸራቸው ጥቅሞች አንዱ፤ ጤናማ ከባቢን መፍጠር ነው። በተለይም በደካማ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ለሚታሙ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሁነኛ መፍትሔ ሆኗል። ይህ ደግሞ በቀጥታ ከነዋሪዎች ጤና ጋር ይገናኛል።ደግሞም በንጹህ አካባቢ የመኖር መብትን ማስጠበቅ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመሥራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሠርተዋል ያሉትም ለዚህ ነው። · በሥራ ዕድል ፈጠራ፡- የኮሪደር ልማት የዘመቻ ሥራ አይደለም።በትንሹ በአንድ ከተማ ወይም አካባቢ ተጀምሮ እየሰፋ ይቀጥላል። በዚህ ሂደት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል ማሰብ አያዳግትም። እንዲሁም የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ፤ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ የመኪና ማቆሚያ፣ ሱቆች እና መሰል ለንግድ ተግባራት እንዲበጁ ተደርገው ነው። የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር የተሣሠረ ልማት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መናገራቸው ይታወሳል። · በገጽታ ግንባታ ረገድ፡- ከተሞች ሲጸዱና ምቹ ሲሆኑ በዐለም ዘንድ መታወቂያ ይሆናሉ። ነዋሪም በኩራት ስለአካባቢው በየሄደበት አምባሳደር ሆኖ ይመሠክራል። ቱሪስቶችንም ይስባሉ። የቆይታ ጊዜያቸውንም ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉ። ዐለም ዐቀፍ፣ አኅጉር ዐቀፍ እና ሀገር ዐቀፍ ጉባዔዎች እንዲካሄድባቸውም እንዲመረጡ ያስችላል። በከተሞች ከሚሠራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት እየተሠራ ነው። ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማት ለዜጎች መቅረቡን ያሳያል። ይህም ኢትዮጵያውያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ተናግረዋል። የተሟላ ብልጽግና የምናረጋግጠው በዚሁ መንገድ ነውም ብለዋል። የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የተመጣጠነ ዕድገት በሁሉም አካባቢ ለማምጣት የገጠር ኮሪደር ልማት መጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የገጠር ኮሪደር ልማት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ፋይዳን ጨምሮ ብዙ ጥቅም አለው፤ ይህም ዘላቂ ልማትና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይጫዎታል። የከተሞች መዋብና ምቹ መሆን ለነዋሪው ነው፤ በቀጥታ ተጠቃሚውም ሕዝቡ። ስለዚህ መንግሥት ከሚያከናውናቸው በተጨማሪ ባለሃብቱ፣የመንግሥትም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ኅብረተሰቡ የኮሪደር ልማትን በተነሳሽነት ለማስፋፋት መትጋት ይጠበቅበታል። #የኮሪደር_ልማት #ኢዜአ #የኢትዮጵያ_ዜና_አገልግሎት #ኢትዮጵያ
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 23, 2026 3370
በዮሐንስ ደርበው ከግንቦት 9 እስከ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … 👉የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ለአገልግሎት ክፍት መሆን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካል እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ የሆነው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል። ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ መሆኑንም ገልጸዋል። ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛልም ብለዋል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፤ በውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ነው ያሉት። 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጎዴ ማዳበሪያ ፋብሪካ ፕሮጀክት ያደረጉት ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎዴ የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራ የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ይህ ሥራ ከመሠረተ-ልማት ግንባታም በላይ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ ዕድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደት ፍጥነት አበረታች መሆኑን ጠቁመው፤ ይህን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በዕቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉ ሲሉም አረጋግጠዋል። 👉የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በተሰኘውና ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችው ትልቅ ድል በተበሰረበት ሀገራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር። በዚሁ ወቅትም፤ የተመለከቱት የዘርፉ እመርታ እጅግ አስደሳች ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል። መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ ዐቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል። ከሁሉም በላይ፤ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራ በሀገር ልጆች ዕውቀትና ክኅሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦችም ላይ መሆን አለበት ነው ያሉት። 👉ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት ባሳለፍነው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐረሪ ክልል የልማት ሥራዎች የጎበኙ ሲሆን በወቅቱም፤ በሐረሪ ክልል የተመለከትነው የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየሩ ረገድ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል። በሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ የተገነቡት ቤቶች የሰዎችን ማደሪያ ከሕጻናትና ከከብቶች ቤት የለዩ፣ የዶሮ እርባታ፣ ሻወርና መፀዳጃ ቤት እንዲሁም የጓሮ የሌማት ትሩፋትን ያካተቱ ሙሉ ፓኬጅ መሆናቸውን ገልጸዋል። የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን ጉልበትና ሀገር በቀል ዕውቀት በመጠቀም፣ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ ያሉትን የማር፣ የወተትና የዶሮ እርባታ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን፤ በከተማው በኢኒሼቲቩ በግለሰብና በመንግሥት ደረጃ ሼዶችን በመገንባት የማር፣ የወተት፣ የእንቁላልና የአሳ መንደሮችን የማቋቋም ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። እንደ ሀገር የአመጋገብ ሥርዓታችንን ከመሠረቱ ለመቀየር እና በምግብ እራስን ለመቻል ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል። የእንስሳት፣ የዶሮና ዓሳ ዝርያ ማሻሻልና መኖ ማቀነባበሪያዎች ላይም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት ይገኛል ነው ያሉት። 👉የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓል የእራት መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽናት፣ የዕድገት እና የጥቁር ሕዝብ የከፍታ ዓርማ ነው ብለዋል። ሀገር ማጽናት የሚቻለው ተቋማትን በማጽናት ነው፤ በዘመናዊ ታሪካችን የገጠሙን የስብራት ወጀቦችን አልፎ፣ የኢትዮጵያን ስምና ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ታሪክ እየጻፈ የተጓዘው አየር መንገዳችን የጽናታችን ግንባር ቀደም ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል። ለሀገራችንም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ በመደገፍ፣ ሀገራችንን በአቪዬሽን መሠረተ ልማት ከፍ በማድረግ፣ የቱሪዝም ዘርፉን በማገዝና በሌሎች ዘርፎች ባለው ግዙፍ አበርክቶው የዕድገታችን ምሰሶ ሆኗልም ነው ያሉት። ይህ ተቋም በሁለት እግሩ እንዲቆም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ መሪዎችና ሠራተኞች ነበሩት፤ አሁንም አሉት፣ ወደፊትም ይኖሩታል። ይህ የተቋሙ አንጡራ ሀብት በመሆኑ የመንግስት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 12795
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 7151
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 12926
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 11394
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳው ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም --
Jun 5, 2026 5253
የጤና ነገር በዮሐንስ ደርበው እንደዋዛ የበርካቶችን በር የሚያንኳኳውን ዲጂታል (ቨርቹዋል) ኦቲዝም እንዴት መከላከል ይቻላል? አንድ ሰው ኦቲዝም አለበት የሚባለው ምን ዓይነት ምልክቶች ሲታዩበት ነው? ከቨርቹዋል ኦቲዝም መንስዔ፣ ምልክቶቹ፣ የሚያስከትለው ጉዳትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች የአዕምሮ ሕክምና ባለሙያ ወ/ሮ መዓዛ መንክር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል። መነሻ ልጆች በአራት የዕድገት ዘርፎች እንደሚያድጉ ያነሱት ወ/ሮ መዓዛ፤ እነሱም የቋንቋ ክኅሎት ዕድገት፣ የአዕምሮ (ነገሮችን፣ ሁኔታዎችን) የመረዳት ዕድገት፣ አካላዊ ዕድገት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕድገት መሆናቸውን ያብራራሉ። በዚህም መሠረት ይላሉ ባለሙያዋ፤ አንድ ልጅ ጤናማ ወይም ሙሉ ዕድገት አለው የሚባለው በአራቱም የዕድገት ደረጃዎች በተመጣጠነ ሁኔታ ሲያድግ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። ምንድንነት? ባለሙያዋ ኦቲዝም በሁለት ተከፍሎ እንደሚታይ ጠቁመው፤ የመጀመሪያው ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕክምና የተረጋገጠ በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች ወይም “ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር” (ዋናው ኦቲዝም) እንደሚባል ይገልጻሉ። ሁለተኛው ቨርቹዋል ኦቲዝም መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ኦቲዝም የሚመስል ምልክቶች የሚያሳዩ ልጆችን የሚገልጽ እንጅ፤ ዋናው ኦቲዝም እንዳልሆነ ያስረዳሉ። ነገር ግን ይላሉ ወ/ሮ መዓዛ፤ አንድ ልጅ ከላይ ከተገለጹት ከአራቱ ሁለቱ በተለይም የቋንቋ ክኅሎት እና የማኅበራዊ መሥተጋብርና የተግባቦት ዕክል ሲገጥመው፤ ዋናው ኦቲዝም አለበት እንደሚባል አስገንዝበዋል። ለቨርቹዋል ኦቲዝም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው? ልጆች ከተወለዱ እስከ 3 ዓመት ባለው ዕድሜያቸው ለተንቃቃሽ ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ቴሌቪዥን (ለስክሪኖች) ለረጅም ሠዓታት በድግግሞሽ ተጋላጭ ሲሆኑ ለኦቲዝም መሰል ምልክቶች (ቨርቹዋል ኢቲዝም) ተጋለጡ ተብሎ እንደሚወሰድ የአእምሮ ሕክምና ባለሙያዋ ተናግረዋል። ይህን ተከትሎም ልጆች ከሰዎች ጋር ባለመቀራረብ፣ በገሃዱ ዓለም የሚደረገውን ነገር ካላማየት የተነሳ ያልተለመዱ (አዳዲስ) ባሕርያትን እንደሚያዳብሩ ጠቁመው፤ እነዚህ ባሕርያትም ኦቲዝም መሰል (ቨርቹዋል ኦቲዝም) መሆናቸውን ይገልጻሉ። ጉዳዩን በምሳሌ ሲያብራሩም፤ ከዕድሜ እኩዮቻቸው ጋር ተግባብቶ መጫወት ምን እንደሆነ አለማወቅ፣ ተረጋግቶ መቀመጥ አለመቻል፣ በገሃዱ ዓለም ለሚደረጉ ነገሮች ትኩረት አለመስጠት፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ለስክሪን እና ዲጂታል ለሆኑ ነገሮች ሱሰኛ መሆን (ምግብ ሲበሉ ሞባይል መያዝ፣ ቴሌቪዥን ዕያዩ መብላት መፈለግ)፣ ማንኛውንም ነገር ሞባይል ወይም ቴሌቪዥን ካልተከፈተ ማድረግ አለመቻል (አለመፈለግ) የሚሉት የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን ነው የዘረዘሩት። ይህን ተከትሎም ይላሉ ባለሙያዋ፤ የቋንቋ ክኅሎታቸው እንደ ዕድሜ እኩዮቻቸው የዳበረ አይሆንም፤ ከዚህም ሲያልፍ ኦቲዝም መሰል ምልክቶች በሚኖሩበት ወቅት በቀላሉ ከማኅበረሰቡ ጋር ለመግባባት በጣም ይቸገራሉ ሲሉ አስገንዝበዋል። የኦቲዝም መንስዔ ምንድን ነው? እንዴት መጣ? የሚለው እስካሁን በመጠናት ላይ መሆኑን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ቨርቹዋል ኦቲዝም ግን መንስዔው እንደሚታወቅ አረጋግጠዋል። መንስዔውም ልጆች ለረጅም ሠዓትና በድግግሞሽ (ለብዙ ጊዜያት) ለስክሪን ተጋላጭ መሆናቸው ነው ይላሉ። ልጆች ቴክኖሎጂን መቼ ይጠቀሙ? እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ ልጆች ከተወለዱ እስከ ሁለት ዓመት በፍጹም እንዳይጠቀሙ ይመከራል። በአንጻሩ ከወላጆቻቸው ጋር እንዲያወሩ፣ አካባቢያቸውን እንዲያዩ፣ በመንቀሳቀስና በመነካካት ገሃዱን ዓለም እንዲረዱ እንደሚመከር አመላክተዋል። ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከሁለት እስከ ስድስት ዓመታቸው፤ ቋንቋን (ንግግርን) የሚያበረታቱ፣ ትምህርት ሰጭ ሆነው ከተገኙ ከአዋቂዎች ጋር በመሆን የጨዋታ ክኅሎትን የሚያዳብሩ ንግግር ያላቸው (መዝሙሮችና ሌሎችንም) በቀን ለ30 ደቂቃ እንዲመለከቱ ማድረግ ይመከራል ብለዋል። ንግግር የሌላቸው ቪዲዮዎች ግን ልጆች ከፊልሙ ዐይተው እንኳን ቋንቋ እንዳይማሩ ስለሚገድቡ ለልጆች ተገቢ አይደሉም ይላሉ። ከሁለት እስከ ስድስት ዓመት ለሆናቸው ግን ትምህርታዊ ጉዳይ ከሆነ እና ልጄ ስነግረው ስላልገባው በስክሪን ሳሳው ሊገባው ይችላል ብለው ወላጆች ሲያስቡ ለዚያውም ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ለማስተማር ብቻ እስከ 30 ደቂቃ በቀን መጠቀም ቢችሉ ጥሩ ነው ብለዋል። እነማን ተጋላጭ ናቸው? ብዙ ጊዜ ወላጆች ባለማወቅ ልጆች ሲንቀሳቀሱ፣ ያገኙትን ሲነካኩ ጥፋት ይከሰታል፣ ይወድቃሉ … በሚል እሳቤ አርፈው እንዲቀመጡ በማሰብ ስልክ ይሰጧቸዋል፤ ቴሌቪዥንም ይከፍቱላቸዋል የሚሉት ወ/ሮ መዓዛ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሉ ልጆች ተጋላች መሆናቸውን አንስተዋል። ስለዚህ ወላጆች ለረጂም ሠዓት እና በተደጋጋሚ ጊዜ ታብሌት፣ ስልክ እና ቴሌቪዥን ለልጆች መክፈት ለቨርቹዋል ኦቲዝም እንደሚያጋልጥ ተገንዝበው፤ የልጆቻቸውን ጤና ከማወክ ቢቆጠቡ መልካም መሆኑን አመላክተዋል። ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መጠቃታቸውን ማወቅ ይቻላል? እንደ ወ/ሮ መዓዛ ማብራሪያ፤ ልጆች በቨርቹዋል ኦቲዝም መያዛቸውን ወላጆችም በቤታቸው ማወቅ ይችላሉ፤ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድም በምርመራ ማወቅ ይቻላል። ወላጆች በቤት ውስጥ መለየት የሚችሉበት ስልትም፤ ቴሌቪዥን ሲጠፋ፣ ሞባይል ሲከለከሉ ልጆች በከፍተኛ ሁኔታ የሚበሳጩ ከሆነ፣ ምግብ አልበላም የሚሉ ከሆነ፤ አልታዘዘም ካሉ፣ ተረጋግተው የማይቀመጡ ከሆነ፣ እየተንቀሳቀሱ ቁጣቸውን የሚገልጹ ከሆነ እነዚህ ምልክቶች ሱስ እንደሆነባቸው ይጠቁማል ይላሉ። በተጨማሪም የንግግር መዘግየት ካለ፣በአካባቢያቸው ስለሚከናወኑ ሁኔታዎች ብዙም ትኩረት የማይሰጡ ከሆነ የቨርቹዋል ኦቲዝም ምልክቶች መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለተሻለ የባለሙያ እገዛ በዚህ ጊዜ ልጆችን ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ እንደሚገባ ይመክራሉ። ሕክምና ቀዳሚው የሕክምና አካል የኦቲዝሙን ዓይነት በምርመራ መለየት መሆኑን ወ/ሮ መዓዛ አስረድተዋል።ይህም ማለት በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች (ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ነው ወይስ ቨርቹዋል ኦቲዝም ነው የሚለው ከተለየ በኋላ ወደ ቀጣዩ ሂደት መሄድ ይገባል ይላሉ። በዚህም መሠረት፤ ልጆ ከስክሪን (ቴሌቪዥን፣ ሞባይል፣ ታብሌት…) እንዲከለከሉ ማድረግ የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያመላከቱት። በተጨማሪም ከቤት ወጥተው ከልጆች ጋር እንዲጫወቱ ብሎም የገሃዱን ዓለም እንቅስቃሴ፣ የአኗኗር ሁኔታ እንዲያዩ እና እንዲረዱ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል። የቋንቋ (ንግግር) መዘግየቱ ከባድ ከሆነ (ከእኩዮቻቸው በጣም ወደ ኋላ የቀሩ ከሆነ) ደግሞ ልጆቹ “ስፒች ቴራፒ” እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባም መክረዋል። አክለውም ወላጆች ልጆችን ወደ ቤተሰብ እንዲሁም ወደ መዝናኛ ስፍራ ይዘዋቸው በመሄድ ከሰዎች ጋር ያላቸውን መቀራረብ እንዲያሳድጉ ትኩረትና ጊዜያቸውን ለልጆች መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ መዓዛ እንዳሉት፤ ከላይ የተጠቀሱት አማራጮች ተደርገው መሻሻል ከሌለ (ልጆቹ ካልተሻላቸው) ዋናው ኦቲዝም (በኦቲዝም ጥላ ሥር ያሉ ልጆች/ኦቲዝም ስፔክትረም ዲስኦርደር) ሊሆን ይችላል ብለዋል። ስለዚህ ለዚህኛው የሚሆነውን የሕክምና ክትትል በባለሙያ ታግዘው ማከናወን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። በአጠቃላይ ግን የኦቲዝም ሕክምና ባብዛኛው ከመድኃኒት ይልቅ በትምህርታዊ ሥልጠና በመታገዝ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፤ የሚድንበትን ጊዜ ማወቅ እንደማቻል አመላክተዋል። በእርግጥ መድኃኒት የሚታዘዝበት ጊዜም እንዳለ ጠቁመው፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ካለ፣ ቤተሰብን የመረበሽ ነገር ካለ፣ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ባሕርይ ሲኖር በባለሙያ ታይቶ ነው ብለዋል። ምክረ ሐሳብ ለቴክኖሎጂ ተጋላጭ መሆን ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ለአጠቃቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተለይም በከተሞች አካባቢ ልጆች እንዳይረብሹ በሚል ሞባይል፣ ቴሌቪዥን፣ ታብሌትን እንደ ሞግዚት የመጠቀም ልማድ መኖሩን አንስተዋል። ይህም በልጆች ጤና ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ወላጆች (ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች) መገንዘብ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ምንም እንኳን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና ጥናት ባይኖርም፤ ከዲጂታል አማራጭና አቅርቦት አኳያ በከተሞች ለቨርቹዋል ኦቲዝም የመጋለጥ ሁኔታው ሰፊ እንደሆነ ይታመናል ሲሉም አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #የጤና_ነገር #ኦቲዝም #ቨርቹዋል
የከተማ ግብርናን ከጤና ሙያው ጋር ያጣመረው ወጣት
May 14, 2026 6141
በቀደሰ ተክሌ (ከሚዛን አማን) የሰው ልጅ የሕይወት ኡደት በጊዜ የታጠረ ነው። የሰውነት ሚዛን ተለክቶ ውብ ሆኖ የሚገኘው ደግሞ በዚህ የጊዜ ምጣኔ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ሰርቶ ተገቢው ቦታ ላይ ሲገኙ ብቻ ነው። ጠንካራ ሰዎች በዕድሜ ዘመናቸው የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመው ስኬት ላይ ይደርሳሉ። ለጊዜ ብዙም ትርጉምና ዋጋ የማይሰጡ ሰዎች ደግሞ እንቅስቃሴያቸውን በጊዜ ስለማይገደብና በዚያው ልክ ተሯሩጠው ስለማይሰሩ ስኬታማ ሳይሆኑ ዘመናቸውን በችግር ያሳልፋሉ። ሰው ሲፈጠር ይህን በማመዛዘን የተሻለውን መንገድ ይጠቀም ዘንድ ደግሞ አዕምሮ ተሰጥቶታል። ማንም ሰው በኑሮ ከመመራት ይልቅ ራሱ ኑሮን መምራት የሚችለው ጠንክሮ ሲሰራ ነው። የአንድ ጠንካራ የሥራ ሰው አንዱ መለኪያ ደግሞ የጊዜ አጠቃቀሙ ነው። ጊዜውን በማብቃቃት ካለው ሥራ ተጨማሪ ሥራ ፈጥሮ የሚሰራና ለበለጠ የሚተጋ ስኬታማ ሕይወትን መምራት ይችላል። በሚዛን አማን ከተማ ኢዜአ ያነጋገርው ወጣት ይህን በተግባር በማረጋገጥ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው። ወጣት ዳዊት ባይቴንስ ይባላል። ከተሰማራበት የጤና ዘርፍ ጎን ለጎን ባለው ትርፍ ጊዜ በከተማ ግብርና ሥራ ተሰማርቶ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ይገኛል። ሰርቶ ለመለወጥ ካላው ፍላጎትና ቁርጠኝነት የተነሳ በሕይወቱ ምንም አይነት ጊዜ እንዲባክንበት አይፈልግም። እያንዳንዷን ሰዓትና ደቂቃ ትርጉም ባለው መልኩ ለሥራ ያውላል። ይህ የመነጨው ደግሞ ከሥራ ወዳድነቱ ነው። ሲሰራ ውሎ ሲሰራ ቢያድር ደከመኝና ሰለቸኝን አያውቅም። ለእዚህ ባህሪው እርሾ የሆነው ደግሞ በልጅነቱ ወላጆቹን በግብርና ሥራ እያገዘ ማደጉ ነው። በትምህርቱም ወደ ኋላ ሳይል ጠንክሮ በመማር ስኬታማነቱን አስመስክሯል። የኮሌጅ ትምህርቱን በፋርማሲ የተመረቀው ወጣቱ በአሁን ወቅት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሆስፒታል በጤና ባለሙያነት እየሠራ ይገኛል። የጤና ተቋም ሥራው ቀንና ማታ በፈረቃ የሚሰራ በመሆኑ ከሆስፒታል ሥራው ውጪ ሲሆን ከተማ ወጥቶ በመዝናናት አሊያም በዋዛ ፈዛዛ የሚያሳልፈው ጊዜ የለውም። ከጤና ሥራው ጎን ለጎን በቤቱ ዙሪያ ያለውን ባዶ መሬት እያለማ ይገኛል። የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን ተከትሎ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ይህን የግብርና ልማት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል። የግብርና ሥራውን የጀመረው በጤና ሙያ ሥራው በወር ከሚያገኘው ደመወዝ ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለማግኘት አስቦ ነው። "የግብርና ምርቱ ለቤት ውስጥ ፍጆታ ባውለው እንኳ ወጪዬን ይቀንሳል" የሚለውም ሌላው መነሻ ምክንያቱ ነበረ። በዚህም ባለው ጠባብ መሬት ላይ ቆስጣ፣ ጥቅል ጎመን፣ ካሮትና መሰል የጓሮ አትክልቶችን አልምቶ በመጠቀም "ምግቤን ከጓሮዬ" የሚለውንም ንቅናቄ በተግባር አሳይቷል። በጓሮ ያለማቸውን ምርቶች ለቤተሰብ ፍጆታ ማዋሉም ከወጪ እንደታደገው ነው የገለጸው። የአካባቢው መሬት ያለስስት ከሚያበቅላቸው ፍራፍሬዎች መካከል ሙዝ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ወጣት ዳዊትም በጓሮ አትክልት የጀመረውን ሥራ በማስፋት በቤቱ ዙሪያ የሙዝ ልማት ስራውን አጠናክሯል። የሙዝ ምርቱም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያም እያቀረበ ነው። ዛፉም ጥላ ሆኖ እያገለገለው ነው። ሁሌም ለተጨማሪ ሥራ የሚተጋው ይህ ባለ ራዕይው ወጣት ምርጥ የቡና ዘር ከግብርና ባለሙያዎች በመውሰድ ችግኝ አዘጋጅቶ ለአርሶ አደሮች ያሰራጫል። አምና የቡና ችግኝ ተከላ ወቅት ከ15 ሺህ በላይ የቡና ችግኞችን በጓሮው አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ሆኗል። ከጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባሻገር በቆሎ በማልማትም ተጠቃሚነቱን እያሳደገ ነው። ወጣት ዳዊት ባለው ጠባብ የከተማ ማሳ ላይ እነዚህን ልማቶች እያከናወነ ያለው በአንድ ጊዜ አይደለም። እንደ የአዝመራው ተስማሚነት አፈራርቆ የማልማት ጥበብንም ተክኗል። በቆሎ ደርሶ የተነሳበት ማሳ ላይ ሌሎች አትክልቶችን ያለማል። በሌላ በኩል ደግሞ ጥምር የእርሻ ሥርዓትን በመከተል በሙዝና ሌሎች ፍራፍሬዎች ስር ባለ ክፍት ቦታ ላይ ቡና ያለማል፤ የአትክልት ችግኞችንም ያዘጋጃል። ይህ ብልህነት የተሞላው የከተማ ግብርና ልማት ሥራው የከተማ ቤቱን የገጠር ሞዴል አርሶ አደር ማሳ አስመስሎታል። ወደፊት የተቀናጀ የግብርና ልማት ጣቢያን የመፍጠር ዓላማ እንዳለው የገለጸው ወጣቱ፣ በቅርቡም በንብ ማነብ ሥራ ውስጥ ለመሰማራት እየተዘጋጀ መሆኑን ነው የተናገረው። ለዚህም የቀፎ ግዥና የቀፎ ማስቀመጫ ቦታ ዝግጅት ሥራ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በገበያ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት መቋቋም የሚቻለው ሰርቶ ውጤታማ ሲኮንና ገቢን ማሳደግ ሲቻል ነው የሚል እምነት አለው። ወጣቱ እንደሚለው ምርት የሚያመርት ሰው እየበዛ ሲመጣ ገበያው ይረጋጋል። በመሆኑም ሰዎች ሁሉንም ነገር ከገበያ ከመግዛት ይልቅ ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ የተወሰነ ምርት በማምረት ለቤት ውስጥ ፍጆታ እንዲጠቀሙ ይመክራል። ከመደበኛ የመንግሥት ሥራው ጎን ለጎን የተሰማራበት የከተማ ግብርና ልማት ሥራ ወጪውን ከመቆጠብ አልፎ ተጨማሪ ገቢ እያስገኘለት በመሆኑ በቀጣይም ልማቱን ለማጠናከር ሞራል እንደሆነው ተናግሯል። እሱ እንደሚለው ከሆነ በአካባቢው በርካታ ወጣቶች የቤተሰቦቻቸውን ማሳ ትተው በከተማ ያለ ሥራ ጊዜያቸውን ሲያሳልፉ ማየት የተለመደ ነው። ነገር ግን ነገን የተሻለ ለማድረግ ዛሬ የወጣትነት ጊዜን ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ይላል። ወጣቶችም ያላቸውን ጉልበትና ጊዜ በመጠቀም ሀብት ማፍራት የሚያስችላቸውን ሥራ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራል። በተለይ የእርሻ መሬት ያላቸው ወጣቶች በግብርና ሥራ ራሳቸውን መለወጥ፣ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ፣ ገበያ ማረጋጋትና በሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ማሳረፍ እንዳለባቸው ነው የገለጸው። የሚዛን አማን ከተማ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ የወጣት ዳዊት ታታሪነት ለብዙዎች ተሞክሮ እንደሚሆን ነው የገለጹት። በተለይ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮችን መሠረት በማድረግ ያከናወናቸው ተግባራት በትንሽ መሬት መስራት ከተቻለ ገበያን ማረጋጋት እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ጽህፈት ቤቱ ወጣቱንና የእሱን ፈለግ ተከትለው የሚሠሩ ወጣቶችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። ኃላፊው እንዳሉት በአሁኑ ወቅትም በሌማት ትሩፋት የሥራ ዘርፎች ወጣቶች በብዛት እንዲሰማሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በራስ ተነሳሽነት ያላቸውን ጊዜ አብቃቅተው ወደልማት የገቡ እንደ ወጣት ዳዊት ያሉ ወጣቶች ቢበራከቱ ለግብርናው ዘርፍ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው አዎንታዊ ሚናም የጎላ ነው። ማንም ሰው ኑሮን አሸንፎ ወጤታማ ለመሆን እንደ ወጣት ዳዊት በሥራ መትጋት ይኖርበታል። ወቅቱ ያለን ጊዜ አብቃቅቶ ተጨማሪ ሥራዎች መስራት የግድ የሚልበት ወቅት ነው። ለብዙዎች በቅጥር ሰርቶ በሚገኝ ገቢ ብቻ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል። ለእዚህም እንደወጣት ዳዊት በዙሪያችን ምን ሀብት አለ በሚል ለይቶ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ጊዜን ከጉልበት ጋር አጣምሮ መጠቀምም እንዲሁ ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። የሰው ልጅ በሕጻንነትና በእርጅናው ዕድሜ የፈለገውን ማድረግ፣ ወጥቶና ወርዶ ሀብት ማፍራት አይችልም። ይህ የሚሆነው በወጣትነትና በጎልማሳነት ዕድሜ ብቻ ነው። በመሆኑም ለነገ ያለምነውን በጊዜው ማሳካት የምንችለው ዛሬ ጠንክረን ስንሰራ ነው። ስለዚህ የወጣትነት ዕድሜያችንን በውጤት ለማጀብ ጠንክረን ልንሠራበት ይገባል። ሥራ ክቡር ከመሆን በላይ ጠንክሮ የሰራውንም ያስከብራል፤ ይለውጣል፤ ሰላም !