ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
በምዕራብ ሸዋ ዞን በመኸር እርሻ ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል
May 9, 2026 26
አምቦ ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በዘንድሮ የመኸር እርሻ ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያየ ሰብል ለማልማት ታቅዶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ደጀኔ ደቡሼ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን በ2018/19 የምርት ዘመን 902 ሺህ 892 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዷል። ከልማቱም ከ34 ነጥብ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ግብ ተይዞ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴም 549 ሺህ 190 ሄክታር መሬት መታረሱን ገልጸው፣ ከዚህ ውስጥም ከ144 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው በበቆሎ እና በማሽላ ዘር መሸፈኑን አስረድተዋል፡፡ በመኸር እርሻ ስራውም ከ300 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የምዕራብ ሸዋ ዞን የህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ጽህፈት ቤት የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ስርጭት ባለሙያ አቶ ዳኛቸው አለማየሁ በበኩላቸው፣ በዞኑ ለመኸር እርሻ እስካሁን ወደ 548 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ የአፈር መዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል። ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርጥ ዘር በህብረት ስራ ማህበራት በኩል ለአርሶ አደሩ መቅረቡንም ተናግረዋል። በዞኑ የአምቦ ወረዳ አርሶ አደር ሙለታ ጉተማ፤ በመኸር እርሻ ወቅት ተገቢውን ምርት ለማግኘት አንድ ሄክታር ማሳቸውን ደጋግመው በማረስ እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በግብርና ባለሙያዎች የሚሰጡ አሰራሮችንና ግብዓቶችን በመጠቀም ጥሩ ምርት ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል። አንድ ሄክታር ተኩል ማሳቸውን ማሽላ፤ ጤፍና ገብስ ለመዝራት ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር አበራ ቶሎሳ ናቸው። አሁን ላይ በበጋ መስኖ ያለሙትን ምርት ሙሉ በሙሉ በማንሳት ወደ መኸሩ እርሻ ስራ መግባታቸውን ጠቁመዋል። በዞኑ ባለፈው መኸር ከለማው ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ 33 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በክልሉ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር 180 ሔክታር መሬት በተለያዩ ችግኞች ይሸፈናል
May 9, 2026 30
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 180 ሔክታር መሬት በተለያዩ ችግኞች እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የደን ልማት እንክብካቤ ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን ስዩም ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክረምቱ ወቅት ለሚከሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ ተግባራዊ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር የደን ሽፋንን በመጨመር፣ የደረቁ ምንጮች እንዲያገግሙ በማድረግ እና የግጦሽ መሬት መጠንን በመጨመር አመርቂ ውጤት ተመዝግቦበታል ነው ያሉት፡፡   በአሁኑ ወቅትም በክልሉ 71 ተራሮችን የማልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በለውጡ አመታት በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት 18 ነጥብ 9 ከመቶ የነበረውን የደን ሽፋን ከ 23 ነጥብ 8 በመቶ በላይ ማድረስ መቻሉንም ተናግረዋል። ይህንን ለማስቀጠልም በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በ180 ሔክታር መሬት በተለያዩ ችግኞች ለመሸፈን እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ለዚህም የችግኝ፣የጉድጓድ እና ሌሎች አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች በበቂ ሁኔታ መደረጉን አመልክተው በአሁኑ ወቅትም የበልግ ወቅት የችግኝ ተከላ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። የችግኝ ተከላው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት ትልቅ አበርክቶ እንዳለው አመልክተው ለክረምት ወቅት ተከላ የሚደረገው ዝግጅት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በዘርፉ የተመዘገበውን ለውጥ ዘላቂነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ሊረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዩኒቨርሲቲው የሚሰሩ የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግር ለማቃለል እና ሀገራዊ እድገትን የሚያፋጥኑ ናቸው
May 9, 2026 59
ደብረ ብርሃን፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሚያወጣቸው የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግር ከማቃለል ባለፈ ሀገራዊ እድገትን ለማፋጠን የሚያግዙ መሆናቸውን አስታወቀ። የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 5ኛውን ዓለም ዓቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ እያካሔደ ነው። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለሰ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ዘርፉን በማጠናከር የአካባቢውን ማህበረሰብ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በቴክኖሎጂና መሰል ዘርፎች ተግባር ተኮር የምርምር ስራዎችን እያካሄደ መሆኑን ነው የተናገሩት። የምርምር ስራዎቹ የማህበረሰቡን ችግር ከማቃለል ባለፈ ሀገራዊ እድገትን በሚያፋጥን አግባብ እንዲተገበሩ አቅዶ እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። የዩኒቨርስቲው ጥናትና ምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ሲሳይ ሙላት (ዶ/ር) በበኩለቸው፤ ዩኒቨርሲቲው ከሀገር ውስጥና ከውጭ የምርምር ተቋማት ጋር በመቀናጀት ሀገር በቀል እውቀቶቸን ጥቅም ላይ ለማዋል የጀመራቸው ተግባራት ተስፋ ሰጪ ናቸው ብለዋል። በኮንፍረንሱ 27 የምርምር ስራዎች የቀረቡ ሲሆን ተግባራዊ እንዲሆኑም በቅንጅት እንደሚሰራም ነው ያመለከቱት። በኮንፍረንሱ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት የማታው አዲስ (ዶ/ር)፤ ለጤናና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውል አዲስ ቴክኖሎጂ ላይ ያደረጉትን የምርምር ስራ አቅርበዋል። የምርምር ኮንፍረንሶች እርስ በእርስ ትስስር በመፍጠር የምርምር ስራዎችን በቅንጅት ወደ ተግባር ለማሸጋገር እንደሚያግዙም አመልክተዋል። ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ኢርፖሴ ኢንስኔ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የምርምር ኮንፍረንሶች የጋራ ሃሳብን በማፍለቅ የሀገርን ኢኮኖሚና ማህበራዊ አቅም ለማሳደግ ያግዛሉ ብለዋል።
በወሰድነው ካርድ ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
May 9, 2026 70
ሚዛን አማን፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ በወሰድነው ካርድ ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ገለጹ። ግንቦት 24 ቀን 2018 ቀን በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዲሳተፉ በልዩ ሁኔታ ካርድ እንዲያወጡ ምርጫ ቦርድ ማድረጉ ይታወሳል። ይህን ዕድል ተጠቅመው ምርጫ ካርድ ያወጡ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በወሰዱት ካርድ ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ኢዜአ ካነጋገራቸው ተማሪዎች መካከል ተማሪ አስታውሰኝ አምሃ በምርጫ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚሳተፍ ገልጾ፣ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ ካርድ እንዲያወጡ ማመቻቸቱ የምርጫውን አሳታፊነት ያሳያል ብሏል። በዘንድሮ ምርጫ በመሳተፍ ለቀጣይ ሀገርን የሚመራ ፓርቲ መምረጥ የሚያስችለውን ዕድል በማግኘቱ መደሰቱን ገልጾ፣ በምርጫ የአንድ ሰው ድምጽ ዋጋ ስላለው ካርዱን በሚገባ እጠቀምበታለሁ ነው ያለው። ተማሪ ነሲማ ሀሰን በበኩሏ ትምህርታቸው ሳይስተጓጎል በምርጫ የሚሳተፉበት እድል መመቻቸቱ የሚበረታታ መሆኑን ጠቁማ፣ ይህም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁሉንም ያሳተፈ ምርጫ ለማካሄድ ቁርጠኛ መሆኑን ያሳያል ብላለች።   የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም ካርድ ወስደው እየተዘጋጁ እንደሆነ የተናገሩት ደግሞ ተማሪ ሺዘመድ አይቼው እና ወንድማገኝ አምቦ ናቸው። ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተመቻቸው ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ተጠቅመው ምርጫ ካርድ እንዳወጡ ገልጸው፣ በጠቅላላ ምርጫው ድምጻቸውን ለፈለጉት ፓርቲ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙ አረጋግጠዋል።   ለእዚህም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሀን እያደረጉት ያለውን ክርክርና የሚያቀርቡትን ማኒፌስቶ በመከታታል እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 31ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል
May 9, 2026 72
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ31ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከመቻል በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኢትዮጵያ ቡና በ42 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቻል በ48 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቡናማዎቹ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አላሸነፉም። በ30ኛ ሳምንት መቻል ከአዳማ ከተማ ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ሁለቱም ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። መቻል ካሸነፈ ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ዝቅ ያደርጋል። በሌላኛው መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመቀሌ 70 እንደርታ ከቀኑ ሰባት ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ36 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በ30 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች፣ መቀሌ 70 እንደርታ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻሉም። ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ እና መቀሌ 70 እንደርታ ደግሞ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ ለማግኘት የሚያደርጉት ነው። ሀዲያ ሆሳዕና ከሃዋሳ ከተማ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ባለፉት አራት ጨዋታዎች ከድል የራቀው ሀዲያ ሆሳዕና በ35 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሃዋሳ ከተማ በ44 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሰባት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ሁለቱም ቡድኖች የአሸናፊነትን መንገድ ለማግኘት ይጫወታሉ። ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከምድረ ገነት ሽሬ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። አዳማ ከተማ በ35 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ምድረ ገነት ሽሬ በ33 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ባለፉት 10 የሊግ ጨዋታዎች ከድል የራቀው አዳማ ከተማ ሶስት ነጥብ ለማግኘት እና ከወራጅ ቀጠና ስፍራ ለመራቅ ይጫወታል። በ30ኛ ሳምንት ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 ያሸነፈው ምድረ ገነት ሽሬ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ወደ ሜዳ ይገባል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 31ኛ ሳምንት እስከ ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ሲዳማ ቡና በ55 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በ14 ጎሎች ይመራል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጫዋቾች የሆኑት አዲስ ግደይ እና ናትናኤል ዳንኤል በተመሳሳይ 10 ግቦች ይከተላሉ።
የሚታይ
በአዲስ አበባ የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስቻሉ ስኬታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 
May 8, 2026 245
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስቻሉ ስኬታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤዉን በዓድዋ ድል መታሰቢያ የምክር ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማው ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማብራሪያቸው፤ በመዲናዋ ለህዝብ በተገባው ቃል መሠረት በሁሉም መስክ ዕድገትን የሚያፋጥን የልማት ስኬት መመዝገቡን አብራርተዋል። ለአብነትም የነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት በመንግስት፣ በመንግስትና በግል አጋርነት፣ በሪል እስቴት፣ በግለሰብና በግለሰብ-ግለሰብ አጋርነት በርካታ ቤቶች መገንባታቸውን ገልጸዋል።   በቀጣይም በፕሮጀክት ግንባታ የተፈጠረውን ውጤታማ ስትራቲጂያዊ አፈፃጸም በማጎልበት የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በማህበራዊ ዘርፍም በጤና መከላከልና አክሞ ማዳን የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት የሚያፋጥን ውጤታማ የጤና ተቋማት ግንባታ ዕውን ማድረግ እንደተቻለ አስረድተዋል። በዚህም በነባር ሆስፒታሎች ማስፋፊያና አዳዲስ የጤና ተቋማት ግንባታ የእናቶችና ሕፃናትን ጨምሮ የዜጎች ጤና አገልግሎት ጥራትንና ተደራሽነትን የሚያስጠብቅ መሠረተ ልማት መገንባቱን አንስተዋል። የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል በተወሰዱ እርምጃዎችም የዋጋ ግሽበትን ወደ ነጠላ አሃዝ ዝቅ ማድረግ ያስቻለ አበረታች ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰዋል። በዚህም የነዋሪዎችን የኑሮ ጫና በቅዳሜና እሁድ ገበያና የገበያ ማዕከላት ሌሎች የምርት አቅርቦት ሥራዎች አቅርቦትና ፍላጎትን ማመጣጠን ያስቻለ ሥራ መሰራቱን አንስተዋል።   የመዲናዋን የትራንስፖርት አገልግሎት ለማሳለጥ በተከናወኑ ተግባራትም በተሽከርካሪ አቅርቦት፣ በመኪና ማቆሚያና በብዙኅን ትራንስፖርት ዘርፍ ወሳኝ ስራ መሰራቱን አንስተዋል። በመጭው አዲስ ዓመትም 500 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ በከንቲባ አዳነች አቤቤ የቀረቡለትን ልዩ ልዩ ሹመቶችን ያጸደቀ ሲሆን የምክር ቤቱን የፍትሕና መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት እጩዎች እንዲሁም የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ዲባባን ሹመት አጽድቋል፡፡ በተጨማሪም ምክር ቤቱ የ9 ነጥብ 94 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት አጽድቋል፡፡
የአዲስ አበባ የስፖርት መሠረተ ልማት ስኬት ዓለም አቀፍ የስፖርት ኹነቶችን የማስተናገድ ዕድል እየፈጠረ ነው 
May 8, 2026 216
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ የስፖርት መሠረተ ልማት ስኬት ዓለም አቀፍ የስፖርት ኹነቶችን የማስተናገድ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዓድዋ ድል መታሰቢያ የምክር ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማው ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጉዳዮች በሰጡት ማብራሪያ፤ በአዲስ አበባ ለሀገር ተረካቢ ሕፃናትና ወጣቶች ምቹ ምኅዳር መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል። በዚህም በሕፃናት ማቆያና በልጆች መጫወቻ ማዕከላት ግንባታ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ጤናማና ብቁ የሚያደርጉ ሰፋፊ የልማት ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። በተለይም ወጣቶች የስፖርታዊ እንቅስቃሴን ባህል በማዳበር ጊዜያቸውን በአካልና በአዕምሮ የሚያዳብሩበት ምኅዳር መፍጠር እንደተቻለ አንስተዋል። በዚህም 495 የነበረውን የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ አሁን ወደ 2 ሺህ በማሳደግ ጤናማና ብቁ የሆነ ተተኪ ስፖርተኛን በማፍራት ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በስፖርት መሰረተ ልማት ማስፋፋትና ለማህበረሰቡ ቅርብ እንዲሆን በማድረግ በተሰራው ስራ ከተማዋን ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮች እንድታስተናግድ እያስቻላት መሆኑን ጠቅሰዋል። ለአብነትም በሚያዝያ ወር ብቻ ሶስት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ሁነቶች በአዲስ አበባ መስተናገዳቸውን አብራርተዋል። ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ወድድሮች የሀገራችንን ባህልና ዕሴት በማስተዋወቅ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን በመፍጠር በወጣቱ ትውልድ ከፍተኛ መነቃቃት እየፈጠረ መሆኑን አስረድተዋል። የአቃቂ ዓለም አቀፍ ሜዳ፣ የአደይ አበባ፣ የአዲስ አበባና አበበ ቢቂላ ዓለም አቀፍ ስታዲየሞች ለመዲናዋ የስፖርታዊ ውድድር አቅም እንደሚሆኑ አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ታመርታለች፤ የተሟላ ሉዓላዊነቷን የማረጋገጥ ጉዞዋን አጠናክራ ትቀጥላለች
May 8, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ታመርታለች፤ የተሟላ ሉዓላዊነቷን የማረጋገጥ ጉዞዋን አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሀሳብ ላለፉት ስድስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አራተኛው የኢትዮጵያ ታምርት ዓለም አቀፍ ኤክስፖ የመዝጊያ መርኃግብር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ተካሂዷል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ በአምራች ኢንዱስትሪው የተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶች የኢትዮጵያን ብልፅግና ያሳዩ ናቸው ብለዋል። በተለዋዋጭ የዓለም ሁኔታ የሀገርን ሉዓላዊነት አስጠብቆ ለመቀጠል ውድድሩን መምራት ካልሆነም ከዓለም እኩል መራመድ ይገባል ብለዋል። በዚህ የዓለም ሁኔታ ራሱን የቻለ ያሸንፋል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በዚህ ረገድ አምራች ኢንዱስትሪው ወሳኝ ዓምድ መሆኑን ጠቅሰዋል። መንግስት ይሄንኑ በሚገባ በመረዳቱ ከመደመር ፍልስፍና እሳቤ የሚመነጩ፣ የፖሊሲ ነጻነትን የሚያጎናጽፉ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በመተግበር ሀገር ከነበረባት ስብራት አገግማ በዓለም አደባባይ ስሟ በበጎ እንዲጠራ እያስቻለ ነው ብለዋል። የሀገር ሉዓላዊነትና ነጻነት በሙሉነት የሚረጋገጠው በጥራት፣ በዓይነት እና በብዛት የኢንዱስትሪ ምርቶችን በራስ ዕውቀት፣ በራስ ክህሎት እና በራስ ቴክኖሎጂ ማምረት ሲችሉ መሆኑን ጠቁመዋል። የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ ምቱ እና ትርታው ጤናማ ካልሆነ፣ በኢኮኖሚ ዘርፉም ሆነ በአጠቃላይ በማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፎች ላይ መዳከምን እንደሚፈጥር ተናግረዋል። መንግሥት በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የታለመውን ዘላቂ ዕድገት እና ተወዳዳሪነት በማረጋገጥ፣ ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚያበረክተውን ድርሻ በፍጥነትና በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማሳደግ ፖሊሲዎችን ማሻሻሉን፣ አሠራሮችን መዘርጋቱን፣ የማበረታቻ ሥርዓት መፍጠሩን፣ አምራች ኢንዱስትሪውን የሚደግፍ ብሔራዊ ካውንስልም ማቋቋሙን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የዚህ ሪፎርም አካል መሆኑን በማንሳት በአራት ዓመታት ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ነው ያሉት። ከግብዓት አቅርቦት፣ ከመሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ ከሎጅስቲክስ አገልግሎት፣ ከሰው ኃይል ልማት እና ምቹ የቢዝነስ ከባቢን ከመፍጠር አንጻር በርካታ ቅንጅታዊ ሥራዎች ተሠርተዋል ብለዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም ሆነ በካውንስሉ በተሠሩ ሥራዎች የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ማሻሻል ተችሏል ብለዋል፡፡ ተኪ ምርቶችን በብዛትና በጥራት ማምረት መጀመሩ ከወጪ ንግድ እና ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንጻርም ብዙ ለውጦች መምጣታቸውን ነው ያነሱት። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሥራ ባህልንና ምርታማነትን ማሻሻሉን፣ የሀገር ውስጥ ምርትን የመሸመት እና የመጠቀም ባህልን ማሳደጉንም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አምራች ኢንዱስትሪው ከራሱ ዘርፍ ዕድገት ባሻገር እንደ ግብርና፣ ኮንስትራክሽን፣ ቱሪዝም እና ጤና ላሉ ሌሎች ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ማኅበራዊ ዘርፎች መነቃቃት እያደረገ ያለው አስተዋጽዖ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ አምራች ኢንዱስትሪውን ከዚህ በላይ ለማሳደግ ኢንዱስትሪያዊ አመለካከት፤ ኢንዱስትሪያዊ ባለ ሀብት እና ኢንዱስትሪያዊ አመራር መኖር እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። ጎንበስ ብሎ አፈር ነክቶ ከብረትና ከማዕድናት ጋር ታግሎ፣ ታሪክን መቀየር ያልተቻለው በዚህ የአመለካከት መዛነፍ የተነሣ ነው በማለት አሁን እሱን እየቀየርን እንገኛለን ብለዋል፡፡ በቀጣይ ዓመት ኤክስፖ የላቁ አዳዲስ እና የተሻሻሉ ምርቶች እንደሚቀርቡም ተስፋቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያም የማምረትና የተሟላ ሉዓላዊነቷን የማረጋገጥ ጉዞዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል በአፅንኦት ተናግረዋል።
ነጻነት እና ህግን አጣምሮ መስራት ያስፈልጋል -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
May 8, 2026 184
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የሚዲያ ተቋማት ነጻነት እና ህግን አጣምረው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት "የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ሀገራዊ የሚዲያ ተቋማት የምክክር መድረክ ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተሳታፊች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፣ በለውጡ ማግስት በሙያቸው ምክንያት የታሰሩ ጋዜጠኞችን መፍታት የመጀመርያ እርምጃ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ እንዲሁም ብሎጎች እንዲከፈቱ እና በኢትዮጵያ የሚዲያ ጃሚንግ ስርዓት እንዲቀር መደረጉን አብራርተዋል፡፡ አሳሪ ህጎች በተለይም የፀረ ሽብር ህጉ ለመናገር እድል የሚሰጥ እንዳልነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም እንዲሻሻል መደረጉን አውስተዋል፡፡ በሪፎርሙ የነበረው ሚዲያን የመክፈት እና ሁሉም ሃሳብ ካለከልካይ እንዲንሸራሸር ማድረግ ቀላል እንዳልነበርም ተናግረዋል፡፡ የሚዲያውን መከፈት ተከትሎ ነጻነትን ማስተዳደር የተሳናቸው ሚዲያዎች እንደነበሩ ጠቁመዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሚዲያዎች ምን መምሰል እንዳለባቸው ለተጠየቁት ጥያቄም በሰጡት ማብራሪያ፤ ሚዲያዎች እውነትን የሚገልጡ እና የጋራ መግባባትን የሚፈጥሩ መሆን እንዳለባቸው አብራርተዋል፡፡ እንዲሁም በውይይት የሚያምኑ እና ሀገራዊ ግቦች ላይ አውቀው የሚሰሩ መሆን ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ ነጻነትን ማስተዳደር እና በህግና በስርዓት የመስራት ልምምድ ላይ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ርዕሰ ጉዳይ መሸጥ የኢትዮጵያ ሚዲያ አንዱ ስንክሳር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ነጻነትን እና ህግን አጣምሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
በዘንድሮው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ57 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ስምምነት ተፈጽሟል
May 8, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦በዘንድሮው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ57 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ስምምነት መፈጸሙን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡ "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሀሳብ ሲካሄድ የቆየው የ2018 የኢትዮጵያ ታምርት ዓለም አቀፍ ኤክስፖ የመዝጊያ መርኃ ግብር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ተካሂዷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ ራሷን መቻሏ የህልውና እና የሉዓላዊነት ጉዳይ እንደሆነ ገልጸዋል። አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ለምርታማነትና ለፈጠራ መጠቀም መጪውን ዘመን መዋጀት መሆኑን ጠቅሰዋል። ለአብነት ያህል በአምስቱም ዘርፎች ከ350 በላይ ኢንዱስትሪዎች መሳተፋቸውን ጠቅሰው፤ ጀማሪ ድርጅቶችን ለማበረታታት በተደረገው ድጋፍ ምርታቸውን እንዲያቀርቡ መደረጉንም ገልጸዋል። በዚህ መርሃ ግብር 20 ስታርት አፖች የፈጠራ ስራቸውን ለጎብኚዎች ማቅረባቸውንም አክለዋል፡፡ አዳዲስ ፈጠራ የተጨመረባቸው የምርት ልማት ውድድሮች በ22 ኢንዱስትሪዎች ለእይታ መቅረባቸውን ጠቅሰው፤ በምግብ ቅምሻ 10 ድርጅቶች ከተለያዩ ግብዓቶች ያመረቷቸውን ልዩ ልዩ ምርቶች በተሳታፊዎች ማስመረጣቸውንም ተናግረዋል፡፡ ከኤክስፖው ከ12 ሺህ በላይ የግብይት ትስስሮች በአምራቾች መካከል መከናወናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በ16 የመንግስት ተቋማትና አምራች ኢንዱስትሪዎች መካከል በተደረገ ትስስር ከ57 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ስምምነት መፈጸሙን ጠቅሰዋል። መንግሥት ለአምራች ዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በኤክስፖው ማሳየት መቻሉን ገልጸዋል። አምራቾች ወደ አፍሪካ ገበያዎች ጭምር መግባት እንዳለባቸው አቅጣጫ የተቀመጠበት፣ የፋይናንስ አቅርቦትን ለማሻሻል ውሳኔ ላይ የተደረሰበት እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ የምርት ሂደትን ለመጀመር መነሳሳት የተፈጠረበት ኤክስፖ ነው ብለዋል። በርካታ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ምርቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁና ከከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩ መደረጉንም ገልጸዋል። የቀጣዩ ዓመት የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከግንቦት 5 እስከ 10 ቀን 2019 ዓ.ም ይካሄዳል ብለዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በወሰድነው ካርድ ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
May 9, 2026 70
ሚዛን አማን፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ በወሰድነው ካርድ ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ገለጹ። ግንቦት 24 ቀን 2018 ቀን በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዲሳተፉ በልዩ ሁኔታ ካርድ እንዲያወጡ ምርጫ ቦርድ ማድረጉ ይታወሳል። ይህን ዕድል ተጠቅመው ምርጫ ካርድ ያወጡ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በወሰዱት ካርድ ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ኢዜአ ካነጋገራቸው ተማሪዎች መካከል ተማሪ አስታውሰኝ አምሃ በምርጫ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚሳተፍ ገልጾ፣ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ ካርድ እንዲያወጡ ማመቻቸቱ የምርጫውን አሳታፊነት ያሳያል ብሏል። በዘንድሮ ምርጫ በመሳተፍ ለቀጣይ ሀገርን የሚመራ ፓርቲ መምረጥ የሚያስችለውን ዕድል በማግኘቱ መደሰቱን ገልጾ፣ በምርጫ የአንድ ሰው ድምጽ ዋጋ ስላለው ካርዱን በሚገባ እጠቀምበታለሁ ነው ያለው። ተማሪ ነሲማ ሀሰን በበኩሏ ትምህርታቸው ሳይስተጓጎል በምርጫ የሚሳተፉበት እድል መመቻቸቱ የሚበረታታ መሆኑን ጠቁማ፣ ይህም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁሉንም ያሳተፈ ምርጫ ለማካሄድ ቁርጠኛ መሆኑን ያሳያል ብላለች።   የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም ካርድ ወስደው እየተዘጋጁ እንደሆነ የተናገሩት ደግሞ ተማሪ ሺዘመድ አይቼው እና ወንድማገኝ አምቦ ናቸው። ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተመቻቸው ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ተጠቅመው ምርጫ ካርድ እንዳወጡ ገልጸው፣ በጠቅላላ ምርጫው ድምጻቸውን ለፈለጉት ፓርቲ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙ አረጋግጠዋል።   ለእዚህም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሀን እያደረጉት ያለውን ክርክርና የሚያቀርቡትን ማኒፌስቶ በመከታታል እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሊ ጁንዋን አነጋገሩ 
May 8, 2026 275
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሊ ጁንዋን አነጋገሩ። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሊ ጁንዋ የተመራ ከፍተኛ የሥራ አማካሪ ቦርድ አባላት ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊው የሚመሩት ከፍተኛ የሥራ አማካሪ ቦርድ አባላት በአዲስ አበባ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።   የጉብኝቱ ዋና ዓላማ ዘላቂ የልማት ግቦች (SDGs) አፈጻጸምን በአህጉራዊ ደረጃ ያለበትን ሁኔታ ለመገምገም መሆኑ ነው የተገለጸው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሊ ጁንዋ ከፕሬዝዳንት ታዬ ጋር ከተወያዩ በኋላ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ከፕሬዚዳንቱ ጋር የነበራቸው ውይይት ውጤታማ ነበር። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ እያስመዘገበችው ያለው አስደናቂ እድገትና የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ መለወጡ እጅግ አበረታች መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ስኬታማ የልማት ጎዳና ላይ መሆኗን የተናገሩት ምክትል ዋና ጸሐፊው፤ ይህ መልካም ተሞክሮም በዓለም አቀፍ መድረክ ቀርቦ በማደግ ላሉ ሀገራት እንደ ትልቅ ትምህርት ሊያገለግል እንደሚችል አስገንዝበዋል። የ2030 አጀንዳን ለማፋጠንና ከ2030 በኋላ ያለውን ዓለም አቀፍ የልማት ግብ ለመቅረጽ ከአፍሪካ ባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረገው ውይይት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።   የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) ዋና ጸሐፊ ክላቨር ጋቴቴ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ስኬታማነት ከመጀመሪያው ጀምሮ ቁልፍ ሚና አላት። ኢትዮጵያ ሂደቱን ከመጀመሪያው ጀምሮ ስትደግፍ መቆየቷን ጠቁመው፤ እ.ኤ.አ. በ2015 ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ጉባኤ የተካሄደው አዲስ አበባ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ እየታየ ያለው ሁለንተናዊ ለውጥና እድገት ቡድኑን እጅግ ማስደመሙንም ገልጸዋል። ለተመዘገበው ስኬትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለፕሬዝዳንቱ አመራር ያላቸውን አድናቆትና ምስጋና አቅርበዋል።  
የምርጫ ሂደቱ በሃሳብ የበላይነት የዴሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት ጥሩ መሰረት እያኖረ ነው
May 8, 2026 215
ጅማ ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምርጫ ሂደቱ በፖሊሲ ክርክር በሃሳብ የበላይነት የዴሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት ጥሩ መሰረት እያኖረ መሆኑን የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ኢትዮጵያ እያካሄደችው ያለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፈውበት በተለያዩ የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ በርከት ያሉ የክርክር መድረኮች እየተካሄዱበትና የምረጡኝ ቅስቀሳ እየተከናወነበት ቀጥሏል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሚያዝያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ 50 ሚሊየን 514 ሺህ 155 መራጮች መመዝገባቸውን መግለጻቸው ይታወሳል። ለምርጫው በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሠማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕውቅና መሰጠቱንም የቦርዱ መረጃ ያመለክታል። በዚሁ መሰረት የምርጫ ሂደቱ የቀጠለ ሲሆን የድምጽ መስጫው እለትም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑን ቦርዱ ያወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል። በምርጫ ሂደቱ እስካሁን ያለውን አጠቃላይ ሁኔታ በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር የተለያዩ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንን አነጋግሯል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የስነ-አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር ፍቃዱ ቶለሳ (ዶ/ር)፤ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ፤ የሂደትና ቀጣይነት ያለው ልምምድ ውጤት ስለመሆኑ ገልጸዋል።   በኢትዮጵያ አካታችና አሳታፊ የፖለቲካ ስርአት እየተፈጠረና የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መልካም ጅምር እየታየበት መሆኑን አንስተዋል። በዚህም መሰረት የዘንድሮው የምርጫ ሂደት በፖሊሲ ክርክር በሃሳብ የበላይነት የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ጥሩ መሰረት እያኖረ መሆኑን ለመመልከት ችለናል ብለዋል። በምርጫው ሂደት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሃሳብ ክርክር እንዳለ ሆኖ በምርጫው መብትን ለመጠቀም ዜጎች በምርጫ ምዝገባ ያሳዩት ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በኢትዮጵያ የዳበረ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባትና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለማጽናት የሚያስችል መሆኑን አንስተው ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ትብብርና ተሳትፎው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል።   በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ሙሉዓለም ሀይለማርያም፤ ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት በህዝብ ይሁንታ ላይ የተመሰረተ የመንግስት ምስረታ የሚካሄድበት የዴሞክራሲ መሰረት መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ አንፃር የዘንድሮው ምርጫ ሂደት እስካሁን መልካም የሚባል የፓርቲዎች እንቅስቃሴ፣ የዜጎች ተሳትፎና የሲቪል ማህበራት ጠንካራ ተሳትፎ የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ባለቤትነትና ተሳታፊነትን የሚያረጋግጥ ተግባር እየተከናወነ ነው
May 8, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ባለቤትነትና ተሳታፊነትን የሚያረጋግጥ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ገለፁ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ከመጡ ከአፋህድ አባላት ጋር ለሶስት ቀናት ያደረገውን ምክክር አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)፤ በሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ያካተተና አሳታፊነትን የሚያረጋግጥ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም በአማራ ክልል የሰላም አማራጭን የተቀበሉ አካላት በሀገራዊ ምክክሩ ተሳታፊ የሚሆኑበት ዕድል መመቻቸቱን ተናግረዋል። የሰላም አማራጭን የተቀበሉ አካላትም አሉኝ የሚሏቸውን 17 አጀንዳዎች በመሰነድ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማስረከባቸውን አስታውቀዋል። ባለፉት ሶስት ቀናት የተሳካ ምክክር መካሄዱን ጠቁመው፤ በቀጣይም ከሌሎች ወገኖች ጋር ተመሳሳይ ምክክር ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የኢትዮጵያን ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአካታችነትና አሳታፊነት መርህ ሁሉም አካል የምክክሩ ባለቤት እንዲሆን ማድረግ የሚያስችል ሥራ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ ማህበሩ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል
May 8, 2026 229
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን የጋምቤላ ክልል ወጣቶች ማህበር አስታወቀ። የጋምቤላ ክልል ወጣቶች ማህበር ያሉትን አደረጃጀቶች በማስተባበር ዘንድሮ ለሚካሄደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በንቃት እንዲሳተፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል። የማህበሩ ስራ አስኪያጅ ወጣት ሰለሞን አሰፋ እንደገለፀው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ መሠረት የሚጥል ነው። በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመሰረተ መንግስት ደግሞ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንደሚኖረው ጠቅሰው ይህም ለዜጎች የጋራ እድገትና ልማት መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል። ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማህበሩ ሌሎች የሲቪል ማህበራትና የወጣቶች አደረጃጀቶች ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም ህዝቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያቀርቧቸውን ፕሮግራሞችና ፖሊሲዎች በአግባቡ በመረዳት በቀጣይ ለሀገሪቱ የሚጠቅም ፓርቲ እንዲመርጡ ማህበሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ማህበሩ ከክልል እስከ ወረዳ ባሉት አደረጃጀቶቹ በመጠቀም ህዝቡ ህገ-መንግስታዊ መብቱን በመጠቀም በጠቅላላ ምርጫው ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ግንዛቤ እየፈጠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተመሳሳይ የሲቪል ማህበራትም ጠቅላላ ምርጫው ነፃ፣ ፍትኃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲከናወን ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ሚናቸው የጎላ መሆኑን ወጣት ሰለሞን ገልጿል።  
ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒነት የሴቶችና የወጣቶች አደረጃጀቶች የድርሻቸውን ይወጣሉ
May 8, 2026 284
ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 30/2018(ኢዜአ)፡-ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ አባሎቻቸው የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን የሲዳማ ክልል የሴቶች እና የወጣቶች አደረጃጀቶች ገለጹ። ኢዜአ በሀዋሳ ከተማ ያነጋገራቸው የክልሉ የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶች እንደገለጹት ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ በተለያየ መንገድ ተሳትፏቸውን ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ ነው፡፡ የክልሉ ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወጣት በቃሉ መሰረት እንዳለው ወጣቱ በምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ ድምጹን ለፈለገው ፓርቲ እንዲሰጥና ለምርጫው ስኬታማነት የበኩሉን እንዲወጣ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም በክልሉ የማህበሩ አባል የሆኑ ወጣቶች በምርጫው መሳተፍ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በወቅቱ እንዲወስዱ መደረጉን ገልጿል። የምርጫ ካርድ መውሰድ ብቻ በቂ አይደለም ያለው ወጣት በቃሉ፣ በድምጽ መስጫው እለትም ድምጻቸውን በነጻነት መስጠት እንዲችሉ የማስገንዘብ ሥራ መሰራቱን ተናግሯል። ህብረተሰቡ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ወጣቶች የመቀስቀስና የማስተማር ሥራ ከመስራቱ ባለፈ ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒነት የበኩሉን እንዲወጣ የማስገንዘብ ስራም መከናወኑን አመልክተዋል። የክልሉ ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ገነት ማርቆስ በበኩላቸው እንዳሉት የክልሉ ሴቶች በምርጫው በንቃት እንዲሳተፉ ለማድረግ በተሰጠው የግንዛቤ ስልጠና በርካቶች ለመራጭነት ብቁ የሚያደርጋቸውን ካርድ ወስደዋል። ከዚህ ባለፈ ፌዴሬሽኑን ወክለው በታዛቢነት የሚያገለግሉ 65 ሴቶችን በመመልመል ከኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ጋር በትብብር ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመዋል። ሴቶች በቤተሰብ ውስጥ ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው ያነሱት ወይዘሮ ገነት፣ ለምርጫው አሳታፊነትና ሰላማዊነት ወጣቶች የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ከቤተሰብ ጀምሮ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ የማስገንዘብ ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል። የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ወጣት ጋማርሳ ዲዳ እንዳለው፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ እስከ ወረዳ ባሉ የወጣት አደረጃጀቶች በቅንጅት እየተሰራ ነው። ወጣቱ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ እንዲወስድ ተደርጓል ያለው ፕሬዚዳንቱ፣ በካርዱም ይበጀኛል የሚለውን ለመምረጥ ዝግጅት እንዲያደርግ የማስገንዘብ ሥራ መሰራቱን ተናግሯል።  
ፓርቲው ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ አድርጓል
May 8, 2026 234
ጎንደር፤ ሚያዚያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጉን በጎንደር ከተማ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ገለጹ፡፡ ፓርቲው በጎንደር ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተሞች 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ አካሄዷል። የምርጫ ቅስቀሳውንና የድጋፍ ሰልፉን የተሳተፉ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች እንደገለፁት፤ ምርጫ ለዘላቂ ሰላም መስፈን ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ ወደፊት የሚመራቸውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በቅስቀሳው የተሳተፉት አቶ ዮሃንስ አንዱአለም እንደገለጹት ብልጽግና ፓርቲ በለውጡ ዓመታት ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን መተግበር ችሏል።፡ ምርጫውን ሰላማዊ፣ ነጻና ተዓማኒ በማድረግ ዘላቂ እድገትን ለማረጋገጥ የመራጩ ህዝብ የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው እርሳቸውም በምርጫው በንቃት እንደሚሳተፉ ገልጸዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ፅጌ ቸኮል በበኩላቸው ለሴቶች መብትና ጥቅም መረጋገጥ የሚሰራውን ፓርቲ ለመምረጥ ራሴን አዘጋጅቻለሁ ብለዋል፡፡ "ምርጫ የሰለጠነ ህዝብ የሚተገብረው የዴሞክራሲ ባህል መገለጫ ነው" ያሉት ወይዘሮ ጽጌ ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ አበራ በሪሁን በበኩላቸው ምርጫ የህዝቦች የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጫ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያን የሚያሻግር ሃሳብና ራእይ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ በመምረጥ የተጀመሩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች እንዲቀጥሉ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ለማሳካት እንደሚሰሩም አመልክተዋል። በምረጡኝ ቅስቀሳው ስነ-ስርዓት ላይም በጎንደር ከተማ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ተሳትፈዋል።    
የአፍሪካውያን አዲሱ የተፅዕኖ ድምፅ በዓላማ የሚመራ የአህጉሪቱንና የትውልዱን ተስፋና ዕድሎች የሚያሳይ መሆን አለበት
May 8, 2026 269
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ) ፦ የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ አህጉራዊ አንድነትን ለመገንባት የሚወሰድ ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ ገለጹ፡፡   ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ(ASMIS-2026) እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ''ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣ የአሕጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶችን ለማስመዝገብ፣ የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር የጋራ ምክክር ይደረግበታል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ፤ ጉባኤው የአህጉሪቱን የዲጂታል የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስን ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።   የፐልስ ኦፍ አፍሪካ መወለድ መነሻ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አርቆ አሳቢ ራዕይ መሆኑን አስታውሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፍሪካ የራሷ ድምጽ እንደሚያስፈልጋትና የራሷን ታሪክ በራሷ ልጆች መተረክ እንዳለባት ባስቀመጡት መሰረት፣ ተቋሙ እውነተኛ አፍሪካዊ ትርክቶችን ለማሰራጨት በግልጽ ተልዕኮ መመስረቱን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በታላቅ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ጠቅሰው ከ30 በላይ በሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ውስጥ ተደራሽነቱን ማስፋቱንና ተቀባይነትን ማግኘቱን ጠቁመዋል። "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው ጉባኤው አህጉራዊ ተፅዕኖን ለማሳደግና ለማነቃቃት ያለመ መሆኑንም አብራርተዋል። የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተዕፅኖ ዘመኑን በዋጀ አዲስ ዕይታ ሊበየን እንደሚገባው በማንሳት፥ ለዚህም በዓላማና በኃላፊነት የሚመራ እንዲሁም ውጤት የሚያመጣ ሊሆን እንደሚገባው አፅንኦት ሰጥተዋል። የዲጂታል ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የአፍሪካን ትርክት ለመቀየር ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የዲጂታል ተጽዕኖን ለማዝናናት ብቻ ሳይሆን ለማስተማር፣ አንድነትን ለማጠናከርና አህጉሪቱን ለመገንባት መጠቀም እንዳለባቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሴቶችን መሪነት የሚያጎላና ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት፣ ብዝበዛና በደል የሚቃወም የዲጂታል ተፅዕኖ መፍጠር እንደሚገባ ጠቅሰው አብሮነትን፣ የትውልዱን ተስፋና ዕድሎች አጉልተው የሚያሳዩ ትርክቶችን ማስፋት እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካን ታላቅነትና ባህል በማስተዋወቅ ወጣቱን ትውልድ ለፈጠራና ለልማት ማነቃቃት እንደሚገባቸውም ጠቁመዋል፡፡ ይህንን አዲስ ንቅናቄ የሰው ዘር መገኛ፣ የአፍሪካ መዲና እና የአህጉሪቱ የጽናት ምልክት ከሆነቸው ሀገር-ኢትዮጵያ መጀመር እንደሚገባም ነው ያነሱት። ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ያላቸውን ተቀባይነት በጥበብ፣ በድፍረት እና ለአፍሪካ ባለ ጥልቅ ፍቅር መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አፍሪካውያን የራሳቸውን ታሪክ እንዲተርኩ ላደረጉት እገዛና ለአህጉሪቱ እድገት ላላቸው ቁርጠኝነት ታላቅ አክብሮታቸውን ገልጸዋል። ለጉባኤው ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ለቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ለኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና ለሌሎችም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ፖለቲካ
በወሰድነው ካርድ ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል
May 9, 2026 70
ሚዛን አማን፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ በወሰድነው ካርድ ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ገለጹ። ግንቦት 24 ቀን 2018 ቀን በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዲሳተፉ በልዩ ሁኔታ ካርድ እንዲያወጡ ምርጫ ቦርድ ማድረጉ ይታወሳል። ይህን ዕድል ተጠቅመው ምርጫ ካርድ ያወጡ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በወሰዱት ካርድ ለሀገርና ለህዝብ የተሻለ ሀሳብ ያለውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ኢዜአ ካነጋገራቸው ተማሪዎች መካከል ተማሪ አስታውሰኝ አምሃ በምርጫ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚሳተፍ ገልጾ፣ ምርጫ ቦርድ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ ካርድ እንዲያወጡ ማመቻቸቱ የምርጫውን አሳታፊነት ያሳያል ብሏል። በዘንድሮ ምርጫ በመሳተፍ ለቀጣይ ሀገርን የሚመራ ፓርቲ መምረጥ የሚያስችለውን ዕድል በማግኘቱ መደሰቱን ገልጾ፣ በምርጫ የአንድ ሰው ድምጽ ዋጋ ስላለው ካርዱን በሚገባ እጠቀምበታለሁ ነው ያለው። ተማሪ ነሲማ ሀሰን በበኩሏ ትምህርታቸው ሳይስተጓጎል በምርጫ የሚሳተፉበት እድል መመቻቸቱ የሚበረታታ መሆኑን ጠቁማ፣ ይህም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁሉንም ያሳተፈ ምርጫ ለማካሄድ ቁርጠኛ መሆኑን ያሳያል ብላለች።   የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም ካርድ ወስደው እየተዘጋጁ እንደሆነ የተናገሩት ደግሞ ተማሪ ሺዘመድ አይቼው እና ወንድማገኝ አምቦ ናቸው። ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተመቻቸው ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ተጠቅመው ምርጫ ካርድ እንዳወጡ ገልጸው፣ በጠቅላላ ምርጫው ድምጻቸውን ለፈለጉት ፓርቲ በመስጠት ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙ አረጋግጠዋል።   ለእዚህም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሀን እያደረጉት ያለውን ክርክርና የሚያቀርቡትን ማኒፌስቶ በመከታታል እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሊ ጁንዋን አነጋገሩ 
May 8, 2026 275
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሊ ጁንዋን አነጋገሩ። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሊ ጁንዋ የተመራ ከፍተኛ የሥራ አማካሪ ቦርድ አባላት ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊው የሚመሩት ከፍተኛ የሥራ አማካሪ ቦርድ አባላት በአዲስ አበባ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።   የጉብኝቱ ዋና ዓላማ ዘላቂ የልማት ግቦች (SDGs) አፈጻጸምን በአህጉራዊ ደረጃ ያለበትን ሁኔታ ለመገምገም መሆኑ ነው የተገለጸው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሊ ጁንዋ ከፕሬዝዳንት ታዬ ጋር ከተወያዩ በኋላ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ከፕሬዚዳንቱ ጋር የነበራቸው ውይይት ውጤታማ ነበር። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ እያስመዘገበችው ያለው አስደናቂ እድገትና የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ መለወጡ እጅግ አበረታች መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ስኬታማ የልማት ጎዳና ላይ መሆኗን የተናገሩት ምክትል ዋና ጸሐፊው፤ ይህ መልካም ተሞክሮም በዓለም አቀፍ መድረክ ቀርቦ በማደግ ላሉ ሀገራት እንደ ትልቅ ትምህርት ሊያገለግል እንደሚችል አስገንዝበዋል። የ2030 አጀንዳን ለማፋጠንና ከ2030 በኋላ ያለውን ዓለም አቀፍ የልማት ግብ ለመቅረጽ ከአፍሪካ ባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረገው ውይይት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።   የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) ዋና ጸሐፊ ክላቨር ጋቴቴ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ስኬታማነት ከመጀመሪያው ጀምሮ ቁልፍ ሚና አላት። ኢትዮጵያ ሂደቱን ከመጀመሪያው ጀምሮ ስትደግፍ መቆየቷን ጠቁመው፤ እ.ኤ.አ. በ2015 ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ጉባኤ የተካሄደው አዲስ አበባ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ እየታየ ያለው ሁለንተናዊ ለውጥና እድገት ቡድኑን እጅግ ማስደመሙንም ገልጸዋል። ለተመዘገበው ስኬትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለፕሬዝዳንቱ አመራር ያላቸውን አድናቆትና ምስጋና አቅርበዋል።  
የምርጫ ሂደቱ በሃሳብ የበላይነት የዴሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት ጥሩ መሰረት እያኖረ ነው
May 8, 2026 215
ጅማ ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምርጫ ሂደቱ በፖሊሲ ክርክር በሃሳብ የበላይነት የዴሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት ጥሩ መሰረት እያኖረ መሆኑን የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ። ኢትዮጵያ እያካሄደችው ያለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፈውበት በተለያዩ የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ በርከት ያሉ የክርክር መድረኮች እየተካሄዱበትና የምረጡኝ ቅስቀሳ እየተከናወነበት ቀጥሏል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሚያዝያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ 50 ሚሊየን 514 ሺህ 155 መራጮች መመዝገባቸውን መግለጻቸው ይታወሳል። ለምርጫው በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሠማሩ 169 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕውቅና መሰጠቱንም የቦርዱ መረጃ ያመለክታል። በዚሁ መሰረት የምርጫ ሂደቱ የቀጠለ ሲሆን የድምጽ መስጫው እለትም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑን ቦርዱ ያወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል። በምርጫ ሂደቱ እስካሁን ያለውን አጠቃላይ ሁኔታ በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር የተለያዩ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንን አነጋግሯል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ የስነ-አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር ፍቃዱ ቶለሳ (ዶ/ር)፤ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ፤ የሂደትና ቀጣይነት ያለው ልምምድ ውጤት ስለመሆኑ ገልጸዋል።   በኢትዮጵያ አካታችና አሳታፊ የፖለቲካ ስርአት እየተፈጠረና የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ መልካም ጅምር እየታየበት መሆኑን አንስተዋል። በዚህም መሰረት የዘንድሮው የምርጫ ሂደት በፖሊሲ ክርክር በሃሳብ የበላይነት የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት ጥሩ መሰረት እያኖረ መሆኑን ለመመልከት ችለናል ብለዋል። በምርጫው ሂደት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሃሳብ ክርክር እንዳለ ሆኖ በምርጫው መብትን ለመጠቀም ዜጎች በምርጫ ምዝገባ ያሳዩት ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም በኢትዮጵያ የዳበረ የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባትና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለማጽናት የሚያስችል መሆኑን አንስተው ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ትብብርና ተሳትፎው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል።   በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ሙሉዓለም ሀይለማርያም፤ ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት በህዝብ ይሁንታ ላይ የተመሰረተ የመንግስት ምስረታ የሚካሄድበት የዴሞክራሲ መሰረት መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ አንፃር የዘንድሮው ምርጫ ሂደት እስካሁን መልካም የሚባል የፓርቲዎች እንቅስቃሴ፣ የዜጎች ተሳትፎና የሲቪል ማህበራት ጠንካራ ተሳትፎ የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።
በሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ባለቤትነትና ተሳታፊነትን የሚያረጋግጥ ተግባር እየተከናወነ ነው
May 8, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ባለቤትነትና ተሳታፊነትን የሚያረጋግጥ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ገለፁ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ከመጡ ከአፋህድ አባላት ጋር ለሶስት ቀናት ያደረገውን ምክክር አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)፤ በሀገራዊ ምክክሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ያካተተና አሳታፊነትን የሚያረጋግጥ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም በአማራ ክልል የሰላም አማራጭን የተቀበሉ አካላት በሀገራዊ ምክክሩ ተሳታፊ የሚሆኑበት ዕድል መመቻቸቱን ተናግረዋል። የሰላም አማራጭን የተቀበሉ አካላትም አሉኝ የሚሏቸውን 17 አጀንዳዎች በመሰነድ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማስረከባቸውን አስታውቀዋል። ባለፉት ሶስት ቀናት የተሳካ ምክክር መካሄዱን ጠቁመው፤ በቀጣይም ከሌሎች ወገኖች ጋር ተመሳሳይ ምክክር ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። የኢትዮጵያን ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአካታችነትና አሳታፊነት መርህ ሁሉም አካል የምክክሩ ባለቤት እንዲሆን ማድረግ የሚያስችል ሥራ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ ማህበሩ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል
May 8, 2026 229
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን የጋምቤላ ክልል ወጣቶች ማህበር አስታወቀ። የጋምቤላ ክልል ወጣቶች ማህበር ያሉትን አደረጃጀቶች በማስተባበር ዘንድሮ ለሚካሄደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በንቃት እንዲሳተፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል። የማህበሩ ስራ አስኪያጅ ወጣት ሰለሞን አሰፋ እንደገለፀው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ መሠረት የሚጥል ነው። በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመሰረተ መንግስት ደግሞ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንደሚኖረው ጠቅሰው ይህም ለዜጎች የጋራ እድገትና ልማት መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል። ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማህበሩ ሌሎች የሲቪል ማህበራትና የወጣቶች አደረጃጀቶች ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም ህዝቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያቀርቧቸውን ፕሮግራሞችና ፖሊሲዎች በአግባቡ በመረዳት በቀጣይ ለሀገሪቱ የሚጠቅም ፓርቲ እንዲመርጡ ማህበሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም ማህበሩ ከክልል እስከ ወረዳ ባሉት አደረጃጀቶቹ በመጠቀም ህዝቡ ህገ-መንግስታዊ መብቱን በመጠቀም በጠቅላላ ምርጫው ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ግንዛቤ እየፈጠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በተመሳሳይ የሲቪል ማህበራትም ጠቅላላ ምርጫው ነፃ፣ ፍትኃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲከናወን ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ሚናቸው የጎላ መሆኑን ወጣት ሰለሞን ገልጿል።  
ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒነት የሴቶችና የወጣቶች አደረጃጀቶች የድርሻቸውን ይወጣሉ
May 8, 2026 284
ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 30/2018(ኢዜአ)፡-ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ አባሎቻቸው የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን የሲዳማ ክልል የሴቶች እና የወጣቶች አደረጃጀቶች ገለጹ። ኢዜአ በሀዋሳ ከተማ ያነጋገራቸው የክልሉ የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶች እንደገለጹት ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ በተለያየ መንገድ ተሳትፏቸውን ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ ነው፡፡ የክልሉ ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወጣት በቃሉ መሰረት እንዳለው ወጣቱ በምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ ድምጹን ለፈለገው ፓርቲ እንዲሰጥና ለምርጫው ስኬታማነት የበኩሉን እንዲወጣ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም በክልሉ የማህበሩ አባል የሆኑ ወጣቶች በምርጫው መሳተፍ የሚያስችላቸውን የምርጫ ካርድ በወቅቱ እንዲወስዱ መደረጉን ገልጿል። የምርጫ ካርድ መውሰድ ብቻ በቂ አይደለም ያለው ወጣት በቃሉ፣ በድምጽ መስጫው እለትም ድምጻቸውን በነጻነት መስጠት እንዲችሉ የማስገንዘብ ሥራ መሰራቱን ተናግሯል። ህብረተሰቡ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ወጣቶች የመቀስቀስና የማስተማር ሥራ ከመስራቱ ባለፈ ለምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒነት የበኩሉን እንዲወጣ የማስገንዘብ ስራም መከናወኑን አመልክተዋል። የክልሉ ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ገነት ማርቆስ በበኩላቸው እንዳሉት የክልሉ ሴቶች በምርጫው በንቃት እንዲሳተፉ ለማድረግ በተሰጠው የግንዛቤ ስልጠና በርካቶች ለመራጭነት ብቁ የሚያደርጋቸውን ካርድ ወስደዋል። ከዚህ ባለፈ ፌዴሬሽኑን ወክለው በታዛቢነት የሚያገለግሉ 65 ሴቶችን በመመልመል ከኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ጋር በትብብር ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመዋል። ሴቶች በቤተሰብ ውስጥ ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው ያነሱት ወይዘሮ ገነት፣ ለምርጫው አሳታፊነትና ሰላማዊነት ወጣቶች የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ከቤተሰብ ጀምሮ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ የማስገንዘብ ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል። የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ወጣት ጋማርሳ ዲዳ እንዳለው፣ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ እስከ ወረዳ ባሉ የወጣት አደረጃጀቶች በቅንጅት እየተሰራ ነው። ወጣቱ በምርጫው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ እንዲወስድ ተደርጓል ያለው ፕሬዚዳንቱ፣ በካርዱም ይበጀኛል የሚለውን ለመምረጥ ዝግጅት እንዲያደርግ የማስገንዘብ ሥራ መሰራቱን ተናግሯል።  
ፓርቲው ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ አድርጓል
May 8, 2026 234
ጎንደር፤ ሚያዚያ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጉን በጎንደር ከተማ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ገለጹ፡፡ ፓርቲው በጎንደር ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተሞች 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ አካሄዷል። የምርጫ ቅስቀሳውንና የድጋፍ ሰልፉን የተሳተፉ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች እንደገለፁት፤ ምርጫ ለዘላቂ ሰላም መስፈን ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ ወደፊት የሚመራቸውን ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል። በቅስቀሳው የተሳተፉት አቶ ዮሃንስ አንዱአለም እንደገለጹት ብልጽግና ፓርቲ በለውጡ ዓመታት ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት መሰረት የጣሉ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶችን መተግበር ችሏል።፡ ምርጫውን ሰላማዊ፣ ነጻና ተዓማኒ በማድረግ ዘላቂ እድገትን ለማረጋገጥ የመራጩ ህዝብ የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው እርሳቸውም በምርጫው በንቃት እንደሚሳተፉ ገልጸዋል። ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ፅጌ ቸኮል በበኩላቸው ለሴቶች መብትና ጥቅም መረጋገጥ የሚሰራውን ፓርቲ ለመምረጥ ራሴን አዘጋጅቻለሁ ብለዋል፡፡ "ምርጫ የሰለጠነ ህዝብ የሚተገብረው የዴሞክራሲ ባህል መገለጫ ነው" ያሉት ወይዘሮ ጽጌ ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሃላፊነት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሌላው የሰልፉ ተሳታፊ አቶ አበራ በሪሁን በበኩላቸው ምርጫ የህዝቦች የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጫ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያን የሚያሻግር ሃሳብና ራእይ ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ በመምረጥ የተጀመሩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎች እንዲቀጥሉ ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ለማሳካት እንደሚሰሩም አመልክተዋል። በምረጡኝ ቅስቀሳው ስነ-ስርዓት ላይም በጎንደር ከተማ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ተሳትፈዋል።    
የአፍሪካውያን አዲሱ የተፅዕኖ ድምፅ በዓላማ የሚመራ የአህጉሪቱንና የትውልዱን ተስፋና ዕድሎች የሚያሳይ መሆን አለበት
May 8, 2026 269
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ) ፦ የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ አህጉራዊ አንድነትን ለመገንባት የሚወሰድ ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ ገለጹ፡፡   ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ(ASMIS-2026) እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ''ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣ የአሕጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶችን ለማስመዝገብ፣ የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር የጋራ ምክክር ይደረግበታል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ፤ ጉባኤው የአህጉሪቱን የዲጂታል የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስን ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።   የፐልስ ኦፍ አፍሪካ መወለድ መነሻ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አርቆ አሳቢ ራዕይ መሆኑን አስታውሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፍሪካ የራሷ ድምጽ እንደሚያስፈልጋትና የራሷን ታሪክ በራሷ ልጆች መተረክ እንዳለባት ባስቀመጡት መሰረት፣ ተቋሙ እውነተኛ አፍሪካዊ ትርክቶችን ለማሰራጨት በግልጽ ተልዕኮ መመስረቱን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በታላቅ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ጠቅሰው ከ30 በላይ በሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ውስጥ ተደራሽነቱን ማስፋቱንና ተቀባይነትን ማግኘቱን ጠቁመዋል። "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው ጉባኤው አህጉራዊ ተፅዕኖን ለማሳደግና ለማነቃቃት ያለመ መሆኑንም አብራርተዋል። የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተዕፅኖ ዘመኑን በዋጀ አዲስ ዕይታ ሊበየን እንደሚገባው በማንሳት፥ ለዚህም በዓላማና በኃላፊነት የሚመራ እንዲሁም ውጤት የሚያመጣ ሊሆን እንደሚገባው አፅንኦት ሰጥተዋል። የዲጂታል ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የአፍሪካን ትርክት ለመቀየር ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የዲጂታል ተጽዕኖን ለማዝናናት ብቻ ሳይሆን ለማስተማር፣ አንድነትን ለማጠናከርና አህጉሪቱን ለመገንባት መጠቀም እንዳለባቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሴቶችን መሪነት የሚያጎላና ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት፣ ብዝበዛና በደል የሚቃወም የዲጂታል ተፅዕኖ መፍጠር እንደሚገባ ጠቅሰው አብሮነትን፣ የትውልዱን ተስፋና ዕድሎች አጉልተው የሚያሳዩ ትርክቶችን ማስፋት እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካን ታላቅነትና ባህል በማስተዋወቅ ወጣቱን ትውልድ ለፈጠራና ለልማት ማነቃቃት እንደሚገባቸውም ጠቁመዋል፡፡ ይህንን አዲስ ንቅናቄ የሰው ዘር መገኛ፣ የአፍሪካ መዲና እና የአህጉሪቱ የጽናት ምልክት ከሆነቸው ሀገር-ኢትዮጵያ መጀመር እንደሚገባም ነው ያነሱት። ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ያላቸውን ተቀባይነት በጥበብ፣ በድፍረት እና ለአፍሪካ ባለ ጥልቅ ፍቅር መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አፍሪካውያን የራሳቸውን ታሪክ እንዲተርኩ ላደረጉት እገዛና ለአህጉሪቱ እድገት ላላቸው ቁርጠኝነት ታላቅ አክብሮታቸውን ገልጸዋል። ለጉባኤው ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ለቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ለኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና ለሌሎችም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ማህበራዊ
የጠቅላይ ፍርድ ቤት የቴክኖሎጂ አሰራር ቀልጣፋና የፍትሕ ተደራሽነትን የሚያጠናክር መሆን አለበት
May 8, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦የጠቅላይ ፍርድ ቤት አገልግሎት የቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓት ቀልጣፋና የፍትሕ አገልግሎት ተደራሽነትን የሚያጠናክሩ መሆን እንዳለበት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የበጀት አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት የበጀት ፍላጎትን አስመልክቶ ከፌዴራል ፍርድ ቤቶች የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።   የቋሚ ኮሚቴው አባላት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የ2018 የዘጠኝ ወራት የበጀት አፈጻጸም፣ የበጀት ጣሪያና ማስተካከያዎች ጋር የተያያዙ ጥያቄና አስተያየቶችን አንስተዋል። የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የፍርድ ቤቶች በጀት የሚሰጡ አገልግሎቶችንና ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘበ ከማድረግ አኳያ ለውጦች መኖራቸውን ገልጸዋል።   የፍርድ ቤት አገልግሎቶችን በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማትና ግብዓት በማሟላት የአገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነትን የሚያስጠብቅ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል። በበጀት አጠቃቀም ሥርዓትም በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት የተቋሙን በጀት በአግባቡ መጠቀም መቻሉን አንስተዋል። የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ለሊሴ ደሳለኝ፤ የዳኝነት አገልግሎትን ቀልጣፋና ግልጽነት የሚያስጠብቅ ውጤታማ የተቋም ማሻሻያና የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቡላ ዋጋሪ፤ የዳኞችን የመኖሪያ ከባቢ፣ የደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ማስተካከያ መደረጉን አንስተዋል። ለዳኞች ምቹ የመኖሪያ አካባቢን ለመፍጠርና የደመወዝና ጥቅማጥቅም ማስተካከያ ሥራዎች እየተከናወኑ በመሆኑ የበጀት ማስተካከያ ማስፈለጉን ገልጸዋል። የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ፉአድ ኪያር፤ የዳኞችን የደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ማስተካከያ መደረጉ የበጀት ማሻሻያ እንዲደረግ ያስቻለ ዐበይት ተግባራት መካከል አንዱ ነው ብለዋል። የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪአ ፍርድ ቤት የአስተዳደርና የሰው ሀብት ዋና ዳይሬክተር አየለ ዳሮርሳ፤ በዲጂታልና የሕንጻ ዕድሳት ሥራ የተቋምን ምቹ የሥራ ከባቢ የሚያላብስ ምኅዳር ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ፤ የፍርድ ቤቶች የበጀት አፈፃጸምና ማስተካከያ መረጃ ግልጽነት ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል። የፍርድ ቤቶች የችሎት ማስቻያ ሕንጻዎችን ጥገና በመደበኛ በጀት በማከናወን ለማጠናቀቅ የበጀት እጥረት እንዳይፈጠር ጥናቶችን በማድረግ ዘላቂ መፍትሔ መስጠት እንደሚያስፈልግም አፅንኦት ሰጥተዋል። የጠቅላይ ፍርድ ቤት አገልግሎት የቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓት ቀልጣፋና የፍትሕ አገልግሎት ተደራሽነትን የሚያጠናክሩ መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።
ነጻነት እና ህግን አጣምሮ መስራት ያስፈልጋል -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
May 8, 2026 184
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ የሚዲያ ተቋማት ነጻነት እና ህግን አጣምረው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት "የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ሀገራዊ የሚዲያ ተቋማት የምክክር መድረክ ተካሄዷል። በመድረኩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተሳታፊች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፣ በለውጡ ማግስት በሙያቸው ምክንያት የታሰሩ ጋዜጠኞችን መፍታት የመጀመርያ እርምጃ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ እንዲሁም ብሎጎች እንዲከፈቱ እና በኢትዮጵያ የሚዲያ ጃሚንግ ስርዓት እንዲቀር መደረጉን አብራርተዋል፡፡ አሳሪ ህጎች በተለይም የፀረ ሽብር ህጉ ለመናገር እድል የሚሰጥ እንዳልነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም እንዲሻሻል መደረጉን አውስተዋል፡፡ በሪፎርሙ የነበረው ሚዲያን የመክፈት እና ሁሉም ሃሳብ ካለከልካይ እንዲንሸራሸር ማድረግ ቀላል እንዳልነበርም ተናግረዋል፡፡ የሚዲያውን መከፈት ተከትሎ ነጻነትን ማስተዳደር የተሳናቸው ሚዲያዎች እንደነበሩ ጠቁመዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሚዲያዎች ምን መምሰል እንዳለባቸው ለተጠየቁት ጥያቄም በሰጡት ማብራሪያ፤ ሚዲያዎች እውነትን የሚገልጡ እና የጋራ መግባባትን የሚፈጥሩ መሆን እንዳለባቸው አብራርተዋል፡፡ እንዲሁም በውይይት የሚያምኑ እና ሀገራዊ ግቦች ላይ አውቀው የሚሰሩ መሆን ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ ነጻነትን ማስተዳደር እና በህግና በስርዓት የመስራት ልምምድ ላይ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ርዕሰ ጉዳይ መሸጥ የኢትዮጵያ ሚዲያ አንዱ ስንክሳር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ነጻነትን እና ህግን አጣምሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
የጤና ነገር …
May 8, 2026 442
በዮሐንስ ደርበው የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽን ምንድነው? ሕጻናት ከተወለዱ እስከ 28 ቀናት ባለው ጊዜ በደማቸው ውስጥ ባክቴሪያ ወደ ተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ሲዛመት የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽን ተብሎ እንደሚጠራ ባለሙያዎች ይናገራሉ። የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽን ምንነት፣ መንስዔና አጋላጭ ምክንያቶችን በተመለከተ የሕጻናት ሕክምና ስፔሻሊስት ዶክተር አበበ የኔዋ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ✍️ የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽን መንስዔ ምንድን ነው? የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽን የሚመጣው በአብዛኛው በባክቴሪያዎች መሆኑን የገለጹት ዶክተር አበበ፤ ከእነዚህ ባክቴሪያዎች መካከልም በዋናነት Escherichia coli, Group B streptococcus እና Listeria monocytogenes የተሰኙት እንደሚገኙበት ለማሳያነት ጠቅሰዋል። ✍️ ለጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽን የሚያጋልጡ ምክንያቶች ይታወቃሉ? የእንሽርት ውኃ ከምጥ 18 ሠዓት እና ከዛ በላይ ቀድሞ መፍሰስ (prolonged premature rupture of membrane)፤ የመውለጃ ጊዜያቸው በተቃረበበት ወቅት የሚከሰት የእናቶች ኢንፌክሽን (chorioamnionitis፣ Urinary tract infection)፤ የተራዘመ ምጥ (prolonged labor)፤ በቂ የእርግዝና ክትትል አለመኖርና ከጤና ተቋም ውጭ (በቤታቸው) መውለድ ወ.ዘ.ተ. እንደ ኢንፌክሽን አጋላጭ ተደርገው ይጠቀሳሉ ብለዋል ዶክተር አበበ። ✍️ የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽንን መከላከል ይቻላል? የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት፤ የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽንን ለመከላከል በዋናነት አጋላጭ ምክንያቶችን በመለየት እነሱ ላይ ቀድሞ መሥራት ነው። በዚህም መሠረት፤ ምጥ ሳይኖር የእንሽርት ውኃ ቀድሞ ከፈሰሰ ቶሎ በሐኪም መታየት እና ሕክምና ማድረግ፣ በእርግዝና ጊዜ የሚከሰት የእናቶች ኢንፌክሽን (የማህፀን፣ የሽንት ቱቦ፣ የሳንባ ካለ) በአግባቡ መታከም፣ የተራዘመ ምጥ ማስወገድ፣ በቂ የእርግዝና ክትትል ማድረግና በጤና ተቋም መውለድ እንደሚገባ መክረው፤ ይህም ህመሙን ቀድሞ ለመከላከል እንደሚረዳ አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ከተወለዱ በኋላ በአራስ ቤታቸው እያሉ ሳል ወይም ሌላ ተላላፊ ህመም ያለበት ሰው እንዳይቀርብ ማድረግና መጠንቀቅ፣ በቤት ውስጥ ጭስ እንዳይኖር ማድረግ እንዲሁም የጨቅላ ሕጻናት አደገኛ ምልክቶችን በየጊዜው መከታተል ያስፈልጋል ሲሉ መክረዋል። የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽን ምልክቶችን ያሳየ ጨቅላ ሕጻን በቶሎ ወደ ጤና ተቋም ከተወሰደና በተገቢው ሁኔታ ከታከመ የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ✍️ የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽን ምልክቶች በውል ይታወቃሉ? የጨቅላ ሕጻናት ምልክቶች አደገኛ ተብለው እንደሚጠሩ የገለጹት ዶ/ር አበበ፤ ቶሎ ቶሎ መተንፈስ፣ ረጅም ሠዓት የሚቆይ ማቃሰት፣ የሰውነት ትኩሳት (መቀዝቀዝ)፣ የሰውነት መንቀጥቀጥ፣ ጡት አለመሳብ፣ መፍዘዝና አለመንቃት፣ ራስን መሳት፣ በጣም ተከታታይና ኃይለኛ ትውከት፣ የዐይንና የሰውነት ቢጫ መሆን፣ የሆድ ከመጠን በላይ መወጠር፣ የከንፈርና የምላስ መጥቆር ከምልክቶቹ መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል። ✍️ የጨቅላ ሕጻናት ኢንፌክሽን እንዴት ይታከማል? • እንደ ዶ/ር አበበ ገለጻ፤ ከላይ የተጠቀሱት አደገኛ ምልክቶች ከታዩ በቶሎ ወደ ጤና ተቋም መውሰድ ያስፈልጋል። • በሕክምና ወቅትም፤ የአተነፋፈስ ሁኔታ ታይቶ ለአተነፋፈሱ እገዛ (ኦክስጅን) ሊሰጥ ይችላል ብለዋል። • ትኩሳት ካለም የትኩሳት ማስታገሻ፣ የሰውነት ሙቀቱ ዝቅ ያለ ከሆነ በማሞቂያ (Radiant warmer) እንዲስተካከል ይደረጋል ሲሉ ገልጸዋል። • የስኳር መጠናቸው ዝቅ ካለም ግሉኮስ (dextrose) እንደሚሰጣቸው አስረድተዋል። • ከደም የሚወሰዱ ምርመራዎች እና ከጀርባ የሚወሰድ ምርመራ (Cerebro spinal fluid analysis & Culture) ማድረግም እንደ ህመሙ ዓይነት የሕክምናው አካል መሆኑን ነው ያስረዱት። • በዋናነትም በመርፌ የሚሰጡ ፀረ-ተኅዋስያን መድኃኒቶችን እንዲወስዱ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።
በክልሉ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቷል
May 8, 2026 113
ቦንጋ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን ተሳትፎ ለማጎልበት እየሰራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሴቶች ፌደሬሽን አስታወቀ። ፌደሬሽኑ ከክልሉ አራት ዞኖች ለተወጣጡ የምርጫ ታዛቢ ሴቶች ዛሬ በቦንጋ ከተማ ስልጠና ሰጥቷል።   ስልጠናውን የሰጡት የፌደሬሽኑ ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ትዕግስት ወርቁ እንደገለጹት፤ ለምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒነት ፌደሬሽኑ የበኩሉን ለመወጣት አደረጃጀቶችን በመጠቀም የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል። በቀጣይም ሴቶች በነቂስ ወጥተው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ እንዲመርጡ የማስተማርና የማስገንዘብ ሥራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በክልሉ 46 ሴቶች ለምርጫ ታዛቢነት በፌደሬሽኑ ተመልምለው የአቅም ግንባታ ስልጠና በተለያዩ ከተሞች እየተሰጣቸው መሆኑን ተናግረዋል። በዛሬው እለትም ከአራት የክልሉ ዞኖች ለተወጣጡ ሴት የምርጫ ታዛቢዎች በቦንጋ ከተማ የተሰጠው ስልጠናም የዚሁ አካል እንደሆነ ጠቅሰው፣ ሰልጣኞችም ባገኙት ግንዛቤ መሰረት የተጣለባቸውን ሀላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል። ጠቅላላ ምርጫው ሰላማዊ፣ ተአማኒና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ ከሸካ ዞን የመጡት ወይዘሮ ፍሬሕይወት ሻረው ናቸው። ከካፋ ዞን እና ከቤንች ሸኮ ዞን የመጡት ወይዘሮ የምስራች ካሳ እና ወይዘሮ አስማረች ሀይሌ፤ የተጣለባቸውን የታዛቢነት ሚና በብቃት በመወጣት ለምርጫው ስኬታማነት የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። ስልጠናው የነበረባቸውን የግንዛቤ ክፍተት የሞላና ለቀጣይ ሥራቸውም አቅም የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢኮኖሚ
በምዕራብ ሸዋ ዞን በመኸር እርሻ ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል
May 9, 2026 26
አምቦ ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በዘንድሮ የመኸር እርሻ ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያየ ሰብል ለማልማት ታቅዶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ። በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ደጀኔ ደቡሼ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን በ2018/19 የምርት ዘመን 902 ሺህ 892 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዷል። ከልማቱም ከ34 ነጥብ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ግብ ተይዞ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴም 549 ሺህ 190 ሄክታር መሬት መታረሱን ገልጸው፣ ከዚህ ውስጥም ከ144 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው በበቆሎ እና በማሽላ ዘር መሸፈኑን አስረድተዋል፡፡ በመኸር እርሻ ስራውም ከ300 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የምዕራብ ሸዋ ዞን የህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ጽህፈት ቤት የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ስርጭት ባለሙያ አቶ ዳኛቸው አለማየሁ በበኩላቸው፣ በዞኑ ለመኸር እርሻ እስካሁን ወደ 548 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ የአፈር መዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል። ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርጥ ዘር በህብረት ስራ ማህበራት በኩል ለአርሶ አደሩ መቅረቡንም ተናግረዋል። በዞኑ የአምቦ ወረዳ አርሶ አደር ሙለታ ጉተማ፤ በመኸር እርሻ ወቅት ተገቢውን ምርት ለማግኘት አንድ ሄክታር ማሳቸውን ደጋግመው በማረስ እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በግብርና ባለሙያዎች የሚሰጡ አሰራሮችንና ግብዓቶችን በመጠቀም ጥሩ ምርት ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል። አንድ ሄክታር ተኩል ማሳቸውን ማሽላ፤ ጤፍና ገብስ ለመዝራት ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር አበራ ቶሎሳ ናቸው። አሁን ላይ በበጋ መስኖ ያለሙትን ምርት ሙሉ በሙሉ በማንሳት ወደ መኸሩ እርሻ ስራ መግባታቸውን ጠቁመዋል። በዞኑ ባለፈው መኸር ከለማው ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ 33 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በአዲስ አበባ የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስቻሉ ስኬታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 
May 8, 2026 245
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የነዋሪዎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስቻሉ ስኬታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤዉን በዓድዋ ድል መታሰቢያ የምክር ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማው ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማብራሪያቸው፤ በመዲናዋ ለህዝብ በተገባው ቃል መሠረት በሁሉም መስክ ዕድገትን የሚያፋጥን የልማት ስኬት መመዝገቡን አብራርተዋል። ለአብነትም የነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት በመንግስት፣ በመንግስትና በግል አጋርነት፣ በሪል እስቴት፣ በግለሰብና በግለሰብ-ግለሰብ አጋርነት በርካታ ቤቶች መገንባታቸውን ገልጸዋል።   በቀጣይም በፕሮጀክት ግንባታ የተፈጠረውን ውጤታማ ስትራቲጂያዊ አፈፃጸም በማጎልበት የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በማህበራዊ ዘርፍም በጤና መከላከልና አክሞ ማዳን የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት የሚያፋጥን ውጤታማ የጤና ተቋማት ግንባታ ዕውን ማድረግ እንደተቻለ አስረድተዋል። በዚህም በነባር ሆስፒታሎች ማስፋፊያና አዳዲስ የጤና ተቋማት ግንባታ የእናቶችና ሕፃናትን ጨምሮ የዜጎች ጤና አገልግሎት ጥራትንና ተደራሽነትን የሚያስጠብቅ መሠረተ ልማት መገንባቱን አንስተዋል። የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል በተወሰዱ እርምጃዎችም የዋጋ ግሽበትን ወደ ነጠላ አሃዝ ዝቅ ማድረግ ያስቻለ አበረታች ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰዋል። በዚህም የነዋሪዎችን የኑሮ ጫና በቅዳሜና እሁድ ገበያና የገበያ ማዕከላት ሌሎች የምርት አቅርቦት ሥራዎች አቅርቦትና ፍላጎትን ማመጣጠን ያስቻለ ሥራ መሰራቱን አንስተዋል።   የመዲናዋን የትራንስፖርት አገልግሎት ለማሳለጥ በተከናወኑ ተግባራትም በተሽከርካሪ አቅርቦት፣ በመኪና ማቆሚያና በብዙኅን ትራንስፖርት ዘርፍ ወሳኝ ስራ መሰራቱን አንስተዋል። በመጭው አዲስ ዓመትም 500 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ በከንቲባ አዳነች አቤቤ የቀረቡለትን ልዩ ልዩ ሹመቶችን ያጸደቀ ሲሆን የምክር ቤቱን የፍትሕና መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት እጩዎች እንዲሁም የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ዲባባን ሹመት አጽድቋል፡፡ በተጨማሪም ምክር ቤቱ የ9 ነጥብ 94 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት አጽድቋል፡፡
ኢትዮጵያ ታመርታለች፤ የተሟላ ሉዓላዊነቷን የማረጋገጥ ጉዞዋን አጠናክራ ትቀጥላለች
May 8, 2026 194
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ታመርታለች፤ የተሟላ ሉዓላዊነቷን የማረጋገጥ ጉዞዋን አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሀሳብ ላለፉት ስድስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አራተኛው የኢትዮጵያ ታምርት ዓለም አቀፍ ኤክስፖ የመዝጊያ መርኃግብር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ተካሂዷል።   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ በአምራች ኢንዱስትሪው የተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶች የኢትዮጵያን ብልፅግና ያሳዩ ናቸው ብለዋል። በተለዋዋጭ የዓለም ሁኔታ የሀገርን ሉዓላዊነት አስጠብቆ ለመቀጠል ውድድሩን መምራት ካልሆነም ከዓለም እኩል መራመድ ይገባል ብለዋል። በዚህ የዓለም ሁኔታ ራሱን የቻለ ያሸንፋል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በዚህ ረገድ አምራች ኢንዱስትሪው ወሳኝ ዓምድ መሆኑን ጠቅሰዋል። መንግስት ይሄንኑ በሚገባ በመረዳቱ ከመደመር ፍልስፍና እሳቤ የሚመነጩ፣ የፖሊሲ ነጻነትን የሚያጎናጽፉ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በመተግበር ሀገር ከነበረባት ስብራት አገግማ በዓለም አደባባይ ስሟ በበጎ እንዲጠራ እያስቻለ ነው ብለዋል። የሀገር ሉዓላዊነትና ነጻነት በሙሉነት የሚረጋገጠው በጥራት፣ በዓይነት እና በብዛት የኢንዱስትሪ ምርቶችን በራስ ዕውቀት፣ በራስ ክህሎት እና በራስ ቴክኖሎጂ ማምረት ሲችሉ መሆኑን ጠቁመዋል። የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ ምቱ እና ትርታው ጤናማ ካልሆነ፣ በኢኮኖሚ ዘርፉም ሆነ በአጠቃላይ በማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፎች ላይ መዳከምን እንደሚፈጥር ተናግረዋል። መንግሥት በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የታለመውን ዘላቂ ዕድገት እና ተወዳዳሪነት በማረጋገጥ፣ ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚያበረክተውን ድርሻ በፍጥነትና በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማሳደግ ፖሊሲዎችን ማሻሻሉን፣ አሠራሮችን መዘርጋቱን፣ የማበረታቻ ሥርዓት መፍጠሩን፣ አምራች ኢንዱስትሪውን የሚደግፍ ብሔራዊ ካውንስልም ማቋቋሙን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የዚህ ሪፎርም አካል መሆኑን በማንሳት በአራት ዓመታት ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ነው ያሉት። ከግብዓት አቅርቦት፣ ከመሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ ከሎጅስቲክስ አገልግሎት፣ ከሰው ኃይል ልማት እና ምቹ የቢዝነስ ከባቢን ከመፍጠር አንጻር በርካታ ቅንጅታዊ ሥራዎች ተሠርተዋል ብለዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም ሆነ በካውንስሉ በተሠሩ ሥራዎች የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ማሻሻል ተችሏል ብለዋል፡፡ ተኪ ምርቶችን በብዛትና በጥራት ማምረት መጀመሩ ከወጪ ንግድ እና ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንጻርም ብዙ ለውጦች መምጣታቸውን ነው ያነሱት። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሥራ ባህልንና ምርታማነትን ማሻሻሉን፣ የሀገር ውስጥ ምርትን የመሸመት እና የመጠቀም ባህልን ማሳደጉንም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አምራች ኢንዱስትሪው ከራሱ ዘርፍ ዕድገት ባሻገር እንደ ግብርና፣ ኮንስትራክሽን፣ ቱሪዝም እና ጤና ላሉ ሌሎች ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ማኅበራዊ ዘርፎች መነቃቃት እያደረገ ያለው አስተዋጽዖ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ አምራች ኢንዱስትሪውን ከዚህ በላይ ለማሳደግ ኢንዱስትሪያዊ አመለካከት፤ ኢንዱስትሪያዊ ባለ ሀብት እና ኢንዱስትሪያዊ አመራር መኖር እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። ጎንበስ ብሎ አፈር ነክቶ ከብረትና ከማዕድናት ጋር ታግሎ፣ ታሪክን መቀየር ያልተቻለው በዚህ የአመለካከት መዛነፍ የተነሣ ነው በማለት አሁን እሱን እየቀየርን እንገኛለን ብለዋል፡፡ በቀጣይ ዓመት ኤክስፖ የላቁ አዳዲስ እና የተሻሻሉ ምርቶች እንደሚቀርቡም ተስፋቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያም የማምረትና የተሟላ ሉዓላዊነቷን የማረጋገጥ ጉዞዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል በአፅንኦት ተናግረዋል።
በዘንድሮው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ57 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ስምምነት ተፈጽሟል
May 8, 2026 168
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦በዘንድሮው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ57 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ስምምነት መፈጸሙን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡ "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሀሳብ ሲካሄድ የቆየው የ2018 የኢትዮጵያ ታምርት ዓለም አቀፍ ኤክስፖ የመዝጊያ መርኃ ግብር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ተካሂዷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ ራሷን መቻሏ የህልውና እና የሉዓላዊነት ጉዳይ እንደሆነ ገልጸዋል። አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ለምርታማነትና ለፈጠራ መጠቀም መጪውን ዘመን መዋጀት መሆኑን ጠቅሰዋል። ለአብነት ያህል በአምስቱም ዘርፎች ከ350 በላይ ኢንዱስትሪዎች መሳተፋቸውን ጠቅሰው፤ ጀማሪ ድርጅቶችን ለማበረታታት በተደረገው ድጋፍ ምርታቸውን እንዲያቀርቡ መደረጉንም ገልጸዋል። በዚህ መርሃ ግብር 20 ስታርት አፖች የፈጠራ ስራቸውን ለጎብኚዎች ማቅረባቸውንም አክለዋል፡፡ አዳዲስ ፈጠራ የተጨመረባቸው የምርት ልማት ውድድሮች በ22 ኢንዱስትሪዎች ለእይታ መቅረባቸውን ጠቅሰው፤ በምግብ ቅምሻ 10 ድርጅቶች ከተለያዩ ግብዓቶች ያመረቷቸውን ልዩ ልዩ ምርቶች በተሳታፊዎች ማስመረጣቸውንም ተናግረዋል፡፡ ከኤክስፖው ከ12 ሺህ በላይ የግብይት ትስስሮች በአምራቾች መካከል መከናወናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በ16 የመንግስት ተቋማትና አምራች ኢንዱስትሪዎች መካከል በተደረገ ትስስር ከ57 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ስምምነት መፈጸሙን ጠቅሰዋል። መንግሥት ለአምራች ዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በኤክስፖው ማሳየት መቻሉን ገልጸዋል። አምራቾች ወደ አፍሪካ ገበያዎች ጭምር መግባት እንዳለባቸው አቅጣጫ የተቀመጠበት፣ የፋይናንስ አቅርቦትን ለማሻሻል ውሳኔ ላይ የተደረሰበት እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ የምርት ሂደትን ለመጀመር መነሳሳት የተፈጠረበት ኤክስፖ ነው ብለዋል። በርካታ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ምርቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁና ከከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩ መደረጉንም ገልጸዋል። የቀጣዩ ዓመት የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከግንቦት 5 እስከ 10 ቀን 2019 ዓ.ም ይካሄዳል ብለዋል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በዩኒቨርሲቲው የሚሰሩ የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግር ለማቃለል እና ሀገራዊ እድገትን የሚያፋጥኑ ናቸው
May 9, 2026 59
ደብረ ብርሃን፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሚያወጣቸው የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግር ከማቃለል ባለፈ ሀገራዊ እድገትን ለማፋጠን የሚያግዙ መሆናቸውን አስታወቀ። የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 5ኛውን ዓለም ዓቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ እያካሔደ ነው። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለሰ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ዘርፉን በማጠናከር የአካባቢውን ማህበረሰብ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በቴክኖሎጂና መሰል ዘርፎች ተግባር ተኮር የምርምር ስራዎችን እያካሄደ መሆኑን ነው የተናገሩት። የምርምር ስራዎቹ የማህበረሰቡን ችግር ከማቃለል ባለፈ ሀገራዊ እድገትን በሚያፋጥን አግባብ እንዲተገበሩ አቅዶ እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። የዩኒቨርስቲው ጥናትና ምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ሲሳይ ሙላት (ዶ/ር) በበኩለቸው፤ ዩኒቨርሲቲው ከሀገር ውስጥና ከውጭ የምርምር ተቋማት ጋር በመቀናጀት ሀገር በቀል እውቀቶቸን ጥቅም ላይ ለማዋል የጀመራቸው ተግባራት ተስፋ ሰጪ ናቸው ብለዋል። በኮንፍረንሱ 27 የምርምር ስራዎች የቀረቡ ሲሆን ተግባራዊ እንዲሆኑም በቅንጅት እንደሚሰራም ነው ያመለከቱት። በኮንፍረንሱ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት የማታው አዲስ (ዶ/ር)፤ ለጤናና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውል አዲስ ቴክኖሎጂ ላይ ያደረጉትን የምርምር ስራ አቅርበዋል። የምርምር ኮንፍረንሶች እርስ በእርስ ትስስር በመፍጠር የምርምር ስራዎችን በቅንጅት ወደ ተግባር ለማሸጋገር እንደሚያግዙም አመልክተዋል። ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ኢርፖሴ ኢንስኔ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የምርምር ኮንፍረንሶች የጋራ ሃሳብን በማፍለቅ የሀገርን ኢኮኖሚና ማህበራዊ አቅም ለማሳደግ ያግዛሉ ብለዋል።
በኢትዮጵያ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ህግ መኖር ለሀገራዊ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ መሰረት ነው
May 8, 2026 181
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ህግ መኖር የሀገርን ቁልፍ መሰረተ ልማቶች በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ መሰረት መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ። ቋሚ ኮሚቴው የቁልፍ መሰረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።   ምክትል ሰብሳቢው ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የረቂቅ አዋጁ መዘጋጀት መሰረተ ልማቶችን ከጥቃት በመከላከል ረገድ ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት እንዳይጎዳ ለማድረግ ያስችላል። ረቂቅ አዋጁ ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ለይቶ ያካተተ መሆኑን አንስተው፤ ተቋማቱ ቴክኖሎጂን የሚጠቀሙ በመሆናቸው ለሳይበር ጥቃት እንዳይጋለጡ በማድረግ ረገድ አዋጁ ትልቅ ውጤት እንደሚያመጣ ተናግረዋል። ሰብሳቢው አክለውም፣ አዋጁ የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል ወሳኝ ሚና እንደሚኖረውና ብሄራዊ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ጠንካራ የህግ ማዕቀፍ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በበኩላቸው፤ ተቋሙ የሀገሪቷን መሰረተ ልማቶች ከመጠበቅ አኳያ በርካታ ፖሊሲዎችን፣ አዋጆችንና ደንቦችን እየተገበረ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።   ይህ ረቂቅ አዋጅ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልጸው፣ በጋራ መስራት በዘርፉ ውጤታማነትን እንደሚያረጋግጥ አመልክተዋል። ዲጂታል ኢኮኖሚን በስፋት መጠቀም በሚገባን ልክ ሊከተሉ የሚችሉ ስጋቶችን ለመከላከልና ተገቢውን ጥበቃ ለማድረግ እንዲሁም ለቁልፍ ተቋማት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ አዋጁ ትልቅ ዕድል ይዞ እንደሚመጣም አስገንዝበዋል። በመድረኩ የተገኙ ባለድርሻ አካላት ረቂቅ አዋጁ የሀገሪቷን ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ለተግባራዊነቱ በጋራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በተጨማሪም በዘርፉ በቂና ብቁ ባለሙያዎችን የማፍራት እንዲሁም መንግስት ከግሉ ዘርፍ ጋር በጋራ የመስራት አስፈላጊነት ላይ አስተያየታቸውንና ማብራሪያ የሚሹ ነጥቦችን አቅርበዋል። ዋና ዳይሬክተሯ ትዕግስት ሀሚድ ለተነሱት ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፤ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ለሳይበር ደህንነት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ በቀጣይ በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። በዘርፉ በቂ የሰው ኃይል እየፈራ መሆኑን አንስተው፣ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ ማህዲ (ዶ/ር) በማጠቃለያቸው፤ አስተማማኝ የሳይበር ደህንነትን በኢትዮጵያ ለማረጋገጥ ከመድረኩ የተገኙ ጠቃሚ ግብዓቶችን በመጠቀም አዋጁን ለተግባራዊነት ለማዘጋጀት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
የአፍሪካን እውነት ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል
May 8, 2026 149
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን እውነት ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎች ገለጹ። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የመጀመሪያው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ይገኛል። ጉባኤውም ኃላፊነት የሚሰማቸው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማጠናከር፣ ትብብርን ለመፍጠርና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ግብን ለማሳካት ያለመ ነው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አፍሪካ የራሷን ትርክት በራሷ ለመገንባት፣የአህጉሪቱን እምነት የሚያሳድጉ ውጤቶችን ለማስመዝገብና የአፍሪካን መለያ ለመፍጠር የጋራ ምክክር ያደርጋሉ።   በጉባኤው ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፣ የኤ.ጂ.ኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገመዳ ኦላና፣ የአፍሪካ ህብረት ተወካዮችና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል። በጉባኤው ላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በማህበራዊ ሚዲያ የይዘት ዝግጅቶች ላይ ያለውን አስተዋጽኦ የሚዳስስ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። በኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የናቹራል ላንጉዌጅ ፕሮሰሲንግ ምርምር ዲቪዥን ዳይሬክተር ሳሙኤል ራህመቶ፤ ቀደም ሲል የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለባለሙያዎች የቴክኒክና የምርምር ሥራ ይውል እንደነበር ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ የማህበረሰቡን የዕለት ተእለት የሥራ እንቅስቃሴ ቀለል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣን ዕድገትም ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቁ የፕሮዳክሽን ሥራዎችን የሚያከናውን ምኅዳር በመፍጠር እንደ ሲኒማ የሚታዩ ምስሎችን መፍጠር እያስቻለ መሆኑን አንስተዋል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት ምስልና ድምፅ የማመንጨት አቅም ዕድገት የይዘት ፈጣሪዎችን ሥራ እያገዘ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለይዘት ዝግጅት የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለአህጉሪቱ ትርክትና ገፅታ ግንባታ ማዋል እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።   የአህጉሪቱን እውነተኛ ባህልና ታሪክ ለዓለም ማህበረሰብ ለመተረክም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዕድሎችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። ሌላኛው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ብራያን ጆታ በበኩሉ፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጠራን በማላቅ የዲጂታል ክህሎትን የሚያበለፅግ የቴክኖሎጂ አማራጭ መሆኑን ገልጿል። በዚህም የአፍሪካን እውነተኛ ገፅታ ለዓለም ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የዲጂታል አማራጭ ክህሎትን በማሳደግ መጠቀም እንደሚያስፈልግ ተናግሯል። ቦትስዋናዊው ታዋቂ የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪ ዊሊያምላስት ኬ.አር.ኤም፤ የይዘት ፈጠራ ሥራዎችን ከገንዘብ ማግኛና ቁጥር ባሻገር ለአህጉሪቱ ትርክት ግንባታ መጠቀም አለብን ብሏል። ለዚህም የሥራ ፍቅር ባህልን በማዳበር የዲጂታል አማራጮችን የአፍሪካን የተሻለ ገፅታና ትርክት በሚያጎላ መልኩ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጿል።
‎ባለፉት ስምንት ዓመታት የሚዲያ ምህዳሩን በዲሞክራሲያዊ አውድ ለመዋጀት በወሰድነው እርምጃ ለሀገር ግንባታ የሚረዳ መሠረት ጥሏል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
May 7, 2026 257
‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት ስምንት ዓመታት የሚዲያ ምህዳሩን በዲሞክራሲያዊ አውድ ለመዋጀት በወሰድነው እርምጃ ለሀገር ግንባታ የሚረዳ መሠረት ጥሏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ''የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ'' በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀውና ባለፉት ዓመታት በሚዲያ ዘርፍና ተቋማት ላይ የተመዘገቡ ስኬቶች በቀረቡበት የምክክር መድረክ ላይ ታድሜ ሀሳቤን አጋርቻለሁ ብለዋል።   ይህ ውጤት እንዲቀጥልም ሚዲያዎች ከዋልታ ረገጥነትና ከጽንፈኝነት ወጥተው በእውነት ላይ የተመሠረተ ትርክት በመገንባት፣ ለጋራ ማንነትና ለብሔራዊ መግባባት በቁርጠኝነት ሊሠሩ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል። ‎ሚዲያዎቻችን በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና በጥናት የታገዘ ጥልቅ ትንተና በማቅረብ፣ ከአርዕስት ሽያጭ ባለፈ ለሀገር አጀንዳዎች ትኩረት መስጠት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። ተግባራቸውም በዓላማ፣ በእይታ፣ በሙያዊ ብቃትና ለህዝብ ቅርብ በመሆን ላይ ተመስርቶ፣ ሚዛናዊነትን በጠበቀ መልኩ ለሀገር ብልጽግና መንገድ ጠራጊና ችግር ፈቺ ሆነው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል በመልዕክታቸው።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 31ኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል
May 9, 2026 72
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ31ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከመቻል በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኢትዮጵያ ቡና በ42 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቻል በ48 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ቡናማዎቹ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አላሸነፉም። በ30ኛ ሳምንት መቻል ከአዳማ ከተማ ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል። ሁለቱም ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። መቻል ካሸነፈ ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ዝቅ ያደርጋል። በሌላኛው መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመቀሌ 70 እንደርታ ከቀኑ ሰባት ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይጫወታሉ። የ16 ጊዜ የሊጉ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ36 ነጥብ 13ኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በ30 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች፣ መቀሌ 70 እንደርታ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻሉም። ጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ እና መቀሌ 70 እንደርታ ደግሞ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት በሚያደርገው ትግል ወሳኝ ሶስት ነጥብ ለማግኘት የሚያደርጉት ነው። ሀዲያ ሆሳዕና ከሃዋሳ ከተማ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ባለፉት አራት ጨዋታዎች ከድል የራቀው ሀዲያ ሆሳዕና በ35 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሃዋሳ ከተማ በ44 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ቡድኑ ባለፉት ሰባት የሊግ ጨዋታዎች አላሸነፈም። ሁለቱም ቡድኖች የአሸናፊነትን መንገድ ለማግኘት ይጫወታሉ። ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከምድረ ገነት ሽሬ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። አዳማ ከተማ በ35 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዟል። ምድረ ገነት ሽሬ በ33 ነጥብ 18ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። ባለፉት 10 የሊግ ጨዋታዎች ከድል የራቀው አዳማ ከተማ ሶስት ነጥብ ለማግኘት እና ከወራጅ ቀጠና ስፍራ ለመራቅ ይጫወታል። በ30ኛ ሳምንት ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 ያሸነፈው ምድረ ገነት ሽሬ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ ወደ ሜዳ ይገባል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 31ኛ ሳምንት እስከ ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ሲዳማ ቡና በ55 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በ14 ጎሎች ይመራል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጫዋቾች የሆኑት አዲስ ግደይ እና ናትናኤል ዳንኤል በተመሳሳይ 10 ግቦች ይከተላሉ።
ለዋንጫው የሚፎካከረው ማንችስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን ይገጥማል
May 9, 2026 84
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 36ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ አምስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ማነችስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን በኢትሃድ ስታዲየም ያስተናግዳል። ማንችስተር ሲቲ በ71 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ብሬንትፎርድ በ51 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በ35ኛ ሳምንት ከኤቨርተን ጋር ሶስት አቻ በመውጣት የዋንጫ እድሉን በራሱ የመወሰን እድል ያጣው ሲቲ ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ለማድረግ ይጫወታል። ማንችስተር ሲቲ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ አለው። በ35ኛ ሳምንት ዌስትሃም ዩናይትድ 3 ለ 0 የረታው ብሬንትፎርድ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የመሳተፍ ተስፋውን ለማለምለም ይጫወታል። በሌላኛው መርሐ ግብር ሰንደርላንድ ከማንችስተር ዩናይትድ በስታዲየም ኦፍ ላይት ይጫወታሉ። ሰንደርላንድ በ47 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። ማንችስተር ዩናይትድ በ64 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ባለፉት ሶስት የሊግ ጨዋታዎች ያላሸነፈው ሰንደርላንድ ወደ ድል መንገድ ለመመለስ ይጫወታል። በ35ኛው ሳምንት ሊቨርፑልን 3 ለ 2 በመርታት የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ዩናይትድ፣ ያለውን ጥንካሬ አዝልቆ ለመቀጠል ይፋለማል። ሊቨርፑል ከቼልሲ ከቀኑ 8 ሰዓት ከ30 በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ሌላኛው ተጠቃሽ መርሐ ግብር ነው። የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ሊቨርፑል በ58 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ቼልሲ በ48 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሊቨርፑል የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ለማረጋገጥ የዛሬው ሶስት ነጥብ ያስፈልገዋል። በአንጻሩ ባለፉት ስድስት የሊግ ጨዋታዎች የተሸነፈው እና ከሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ውጪ የሆነው ቼልሲ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል። ፉልሃም ከቦርንማውዝ፣ ብራይተን ከዎልቭስ በተመሳሳይ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የአዲስ አበባ የስፖርት መሠረተ ልማት ስኬት ዓለም አቀፍ የስፖርት ኹነቶችን የማስተናገድ ዕድል እየፈጠረ ነው 
May 8, 2026 216
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ የስፖርት መሠረተ ልማት ስኬት ዓለም አቀፍ የስፖርት ኹነቶችን የማስተናገድ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዓድዋ ድል መታሰቢያ የምክር ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማው ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጉዳዮች በሰጡት ማብራሪያ፤ በአዲስ አበባ ለሀገር ተረካቢ ሕፃናትና ወጣቶች ምቹ ምኅዳር መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል። በዚህም በሕፃናት ማቆያና በልጆች መጫወቻ ማዕከላት ግንባታ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ጤናማና ብቁ የሚያደርጉ ሰፋፊ የልማት ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። በተለይም ወጣቶች የስፖርታዊ እንቅስቃሴን ባህል በማዳበር ጊዜያቸውን በአካልና በአዕምሮ የሚያዳብሩበት ምኅዳር መፍጠር እንደተቻለ አንስተዋል። በዚህም 495 የነበረውን የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ አሁን ወደ 2 ሺህ በማሳደግ ጤናማና ብቁ የሆነ ተተኪ ስፖርተኛን በማፍራት ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በስፖርት መሰረተ ልማት ማስፋፋትና ለማህበረሰቡ ቅርብ እንዲሆን በማድረግ በተሰራው ስራ ከተማዋን ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮች እንድታስተናግድ እያስቻላት መሆኑን ጠቅሰዋል። ለአብነትም በሚያዝያ ወር ብቻ ሶስት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ሁነቶች በአዲስ አበባ መስተናገዳቸውን አብራርተዋል። ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ወድድሮች የሀገራችንን ባህልና ዕሴት በማስተዋወቅ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን በመፍጠር በወጣቱ ትውልድ ከፍተኛ መነቃቃት እየፈጠረ መሆኑን አስረድተዋል። የአቃቂ ዓለም አቀፍ ሜዳ፣ የአደይ አበባ፣ የአዲስ አበባና አበበ ቢቂላ ዓለም አቀፍ ስታዲየሞች ለመዲናዋ የስፖርታዊ ውድድር አቅም እንደሚሆኑ አንስተዋል።
ሩዋንዳ የዓለም አቀፍ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን ትሮፊ የዞን 5 ውድድር አሸናፊ ሆነች
May 8, 2026 124
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው የዓለም አቀፍ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን (IHF) ትሮፊ 2026 የዞን 5 የምስራቅ አፍሪካ ውድድር በሩዋንዳ አሸናፊነት ተጠናቋል። በሁለቱም የዕድሜ እርከኖች ማለትም ከ20 ዓመት እና ከ18 ዓመት በታች በተደረጉት ጨዋታዎች ሩዋንዳ የበላይነቱን በመያዝ የሁለቱም ምድብ ሻምፒዮን መሆን ችላለች። ከ20 ዓመት በታች የፍጻሜ ጨዋታ፣ ሩዋንዳ አስተናጋጇን ኢትዮጵያን አስተናግዳለች። ጨዋታው እጅግ ተቀራራቢና በፉክክር የታጀበ የነበረ ሲሆን፣ በመጨረሻም ሩዋንዳ 39 ለ 37 በሆነ ጠባብ የግብ ልዩነት ኢትዮጵያን በማሸነፍ ዋንጫውን አንስታለች። በዚህ የምድብ ፉክክር ኬንያ የሦስተኛነት ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። በተመሳሳይ በ18 ዓመት በታች የዕድሜ ክልል በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ሩዋንዳ የብሩንዲ አቻዋን በማሸነፍ ሁለተኛ ድሏን አስመዝግባለች። ለሦስተኛ ደረጃ በኬንያ እና በዩጋንዳ መካከል በተደረገው ጨዋታ ደግሞ ኬንያ ድል ቀንቷታል። ይህ ውጤት ሩዋንዳ በሁለቱም የዕድሜ ዘርፎች የቀጣናው ቁንጮ መሆኗን ያረጋገጠችበት ሆኗል። በአጠቃላይ ከሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው ውድድር ላይ ስምንት ሀገራት ተሳትፈዋል። በዚህም መሰረት አሸናፊዋ ሩዋንዳ በቀጣይ በሚካሄደው የአፍሪካ አህጉራዊ የእጅ ኳስ ውድድር ላይ ቀጣናውን ወክላ እንደምትሳተፍ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
አካባቢ ጥበቃ
በክልሉ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር 180 ሔክታር መሬት በተለያዩ ችግኞች ይሸፈናል
May 9, 2026 30
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 1/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 180 ሔክታር መሬት በተለያዩ ችግኞች እንደሚሸፈን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የደን ልማት እንክብካቤ ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን ስዩም ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክረምቱ ወቅት ለሚከሔደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ ተግባራዊ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር የደን ሽፋንን በመጨመር፣ የደረቁ ምንጮች እንዲያገግሙ በማድረግ እና የግጦሽ መሬት መጠንን በመጨመር አመርቂ ውጤት ተመዝግቦበታል ነው ያሉት፡፡   በአሁኑ ወቅትም በክልሉ 71 ተራሮችን የማልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በለውጡ አመታት በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት 18 ነጥብ 9 ከመቶ የነበረውን የደን ሽፋን ከ 23 ነጥብ 8 በመቶ በላይ ማድረስ መቻሉንም ተናግረዋል። ይህንን ለማስቀጠልም በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በ180 ሔክታር መሬት በተለያዩ ችግኞች ለመሸፈን እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ለዚህም የችግኝ፣የጉድጓድ እና ሌሎች አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች በበቂ ሁኔታ መደረጉን አመልክተው በአሁኑ ወቅትም የበልግ ወቅት የችግኝ ተከላ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። የችግኝ ተከላው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት ትልቅ አበርክቶ እንዳለው አመልክተው ለክረምት ወቅት ተከላ የሚደረገው ዝግጅት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በዘርፉ የተመዘገበውን ለውጥ ዘላቂነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ሊረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዞኑ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል
May 8, 2026 173
ጊምቢ፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ በምእራብ ወለጋ ዞን ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታቸው የጎላ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ፍቅሩ ብርሃኑ እንዳሉት በዞኑ ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል። ከችግኞቹም መካከል ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታቸው የጎሉ የቡና፣ የአቮካዶ፣ የማንጎ፣ የፓፓያ እና ሌሎች እንደሚገኙበት አስረድተዋል። የችግኝ ተከላው በበጋ ወራት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ፣ ለእንስሳት መኖ እንዲውልና ለም አፈር በጎርፍ እንዳይወሰድ ለመከላከል ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱ ተገልጿል።   ይህም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ችግኞቹን በበጋ ወራት በተከናወኑ የተለያዩ የእርከን ስፍራዎችና የተመረጡ ቦታዎች ለመትከልም እስካሁን ከ117 ሚሊዮን በላይ ጉድ ጓዶች ቁፋሮ መከናወኑን አቶ ፍቅሩ ጠቅሰዋል። ስራውን ለማሳካትም አርሶ አደሩን በማሳተፍ መከናወኑን የጠቀሱት ሀላፊው፤ የግብርና ባለሙያች ድጋፍና ክትትል ስራዎች መጠናከራችውን አንስተዋል። ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል መዘጋጀታቸውን የጠቀሱት ደግሞ የጊምቢ ወረዳ አርሶ አደር ዋኬኔ አምሳሉ ናቸው። ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞችን ጽድቀት መጠን ለማሳደግ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን በመንከባከብ ከሰውና እንስሳት ንክኪ መጠበቃቸውን ተናግረዋል። ዘንድሮም በመንግስት ከሚለሙት ችግኞች ባለፈ እሳቸው በግላቸው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞችን ማፍላታቸውን ጠቁመዋል። ከዚህ በፊት ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት ባለመስጠታቸው ያጡትን ምርታማነት በሚያካክስ መልኩ በመጪዉ ክረምት የሚተከሉ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች በብዛት ማዘጋጀታቸው የገለጹት የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ለሊሳ ኤቢሳ ናቸው። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ በተሰራው ስራ በርካታ ጥቅም በማግኘታቸውም ስራውን ለማስቀጠል ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የአረንጓዴ አሻራ ልማት ህብረተሰቡን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ አድርጓል
May 8, 2026 175
ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 30/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞች የክልሉን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ ህብረተሰቡን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረጋቸውን የክልሉ አካባቢና ደን ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢኒሼቲቭ የተራቆቱ አካባቢዎችን አረንጓዴ በማልበስና የአካባቢን ሥነ ምህዳር በማስተካከል አርሶ አደሩን ተጠቃሚ እያደረገ ነው።   የአማራ ክልል አካባቢና ደን ጥበቃ ባለስልጣን ሃላፊ ተስፋሁን አለምነህ ለኢዜአ እንደገለጹት የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በክልሉ ከተጀመረ ወዲህ በክልሉ የደን ሽፋን ላይ አበረታች ለውጥ ታይቷል። ለዚህም ባለፉት ዓመታት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞች የክልሉን የደን ሽፋን ቀደም ሲል ከነበረበት 13 ነጥብ 8 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 18 ነጥብ 9 በመቶ ማሳደጋቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል።   ልማቱ የተራቆቱ አካባቢዎች በአረንጓዴ እንዲሸፈኑ፣ የአፈር መሸርሸር እንዲቀርና ለምነቱ እንዲጨምር እንዲሁም የከርሰና የገጸ ምድር ውሃ እንዲጨምር አስችሏል ብለዋል። በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በለሙ አካባቢዎች አርሶ አደሩ የእንስሳት መኖን ጨምሮ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ቸግኞችን በመትከል ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱንም አመልክተዋል። በተለይ መርሀ ግብሩ በእንስሳት እርባታ፣ በእንስሳት ማድለብ፣ በወተት ልማትና በንብ ማነብ ሥራ ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ነው ያስታወቁት።   በክልሉ ግብርና ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር እስመለዓለም ምህረት በበኩላቸው፣ በዘንድሮ ክረምትም የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል አረንጓዴ አሻራን አጠናከሮ ለማስቀጠል ዝግጅት እየተደረገ ነው። እስካሁንም ዘንድሮ ከሚተከለው አጠቃላይ ችግኝ 94 በመቶ የሚሆነው ተፈልቶ ለተከላ መዘጋጀቱን ጠቁመው፣ ለችግኝ ተከላም ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ተዘጋጅቷል ብለዋል። በአማራ ክልል ባለፈው የክረምት ወቅት ከተተከሉ አጠቃላይ ችግኞች ውስጥ 86 በመቶ የሚሆኑት መጽደቃቸውን በመጀመሪያ ዙር በተካሄደ ቆጠራ መረጋገጡን ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
በክልሉ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ከ68 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይሸፈናል
May 7, 2026 288
ቦንጋ፤ሚያዝያ 29/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ከ68 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለመሸፈን ታቅዶ የችግኝ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሀገሪቱ ከፍተኛ የደን ሽፋንና የተፈጥሮ ሀብት ከሚገኝባቸው አካባቢዎች አንዱ ነው። ክልሉ በየዓመቱ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚያከናውናቸው የችግኝ ተከላ ስራዎች፣ ነባር ደኖችን ከመጠበቅ ባለፈ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ለማልማትና የብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።   የዘንድሮው የ68 ሺህ ሄክታር መሬት ሽፋን ዕቅድም ይህንን ክልላዊና ሀገራዊ የአየር ንብረት ለውጥ የመቋቋም ስትራቴጂ አካል ያደረገ ነው። የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው እንደገለጹት፤ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡ ለዚህም ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች የማዘጋጀትና በቴክኖሎጂ የታገዘ የተከላ ቦታ ልየታና መረጃ የማሰባሰብ ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ከ68 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በደንና በሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ችግኞች ለመሸፈን የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና የስራ እድል በመፍጠር የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የካፋ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት መምሪያ ምክትል ሀላፊና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ታሪኩ ወልደ ሚካኤል በበኩላቸው፣ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ዝግጅት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።   በዞኑ የፍራፍሬ፣ የሻይ፣ የቡናና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ለዚህም በ539 የችግኝ ጣቢያዎች ዘር የማፍሰስና የችግኝ እንክብካቤ ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል። የተዘጋጁ ችግኞችም በ36 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የሚተከሉ ሲሆን ቦታ የመለየት እና መረጃ የማደራጀት ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። አርሶ አደሮችም፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ፀድቀው ውጤት እያሳዩ መሆናቸውን ገልፀው፣ የመርሃግብሩ መጀመር ደንን በአግባቡ ለመጠበቅ ትልቅ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል።   በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ተከላ መርሃግብር የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል። የሚተከሉ ችግኞች ፀድቀው አገልግሎት እንዲሰጡ መንከባከብ አስፈላጊ መሆኑን የጠቆሙት አርሶአደሮቹ ፣ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ በርካታ ጥቅም እያገኙ እንደሆነም ገልፀዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት ይገባል 
Apr 28, 2026 1013
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የአህጉሪቷን የልማት ግቦች ለማሳካት የአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራትን የፖሊሲ አቅጣጫ አሰናስሎ መምራት እንደሚገባ የሕብረቱ ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃጸም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 ጎን ለጎን የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው።   የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድን ሀገር በቀል በማድረግ አካታች ዕድገትና ዘላቂ የኢኮኖሚ ሽግግርን የሚያፋጥን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ገልጸዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራትም ብሔራዊ የልማት ዕቅዶችን ከአጀንዳው ጋር በማጣጣም የበጀት ድልድልና የፖሊሲ እርምጃዎችን ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካ አጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦች የበለጸገች አህጉርን እውን ለማድረግም የአባል ሀገራት ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። የአጀንዳ 2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን በማሳካት የተሳለጠ የለውጥ ሽግግርን ለመፍጠርም ጠንካራና የተሰናሰለ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና አህጉራዊ የፖሊሲ ፍሰት ሊኖር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ለዚህም የመንግሥታት፣ የግሉ ዘርፍና የልማት አጋሮች በወሳኝ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ የሚኖራቸውን ትብብርና ቅንጅት የሚያበረታታ ምኅዳር መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።   የዑጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትርና ተሰናባቿ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ ቢሮ ሊቀ-መንበር ሮቢናህ ናባንጃ በበኩላቸው፤ የአፍሪካውያን ድምፅ በወሳኝ የዓለም መድረኮች ላይ መንፀባረቅ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ መድረኮች በከፍተኛ ደረጃ ከሚደረግ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ባለፈ በወሳኝ ስትራቴጂክ ሂደቶች ላይ በንቃት መሳተፍ ይገባቸዋል ብለዋል። የአፍሪካ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካትም ሎጂስቲክስ፣ ትራንስፖርትና መሰል የትኩረት ዘርፎች ላይ በስፋት በመሰማራት ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች ነው
Apr 28, 2026 556
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የአጀንዳ 2030 እና 2063 ዘላቂ የልማት ዕቅዶችን በመተግበር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ ገለጹ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ሕብረት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር "የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን ለማሳካት የተቀናጀና አሻጋሪ አካሄድ መከተል" በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መካሄድ ጀምሯል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ጉባኤ የአፍሪካ ሕብረትን የአጀንዳ 2030 እና 2063 የዘላቂ የልማት ግቦችን አፈፃፀም ይገመግማል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊክ ሀዳዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አጀንዳ 2030 እና 2063 በትይዩ የሚሄዱ ሳይሆን እርስ በርስ የሚደጋገፉ ናቸው። በአፍሪካ አካታች ዕድገትና ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ሽግግር ለመፍጠር ወሳኝ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት የሁለተኛውን የአሥር ዓመት የአጀንዳ 2063 የትግበራ ዕቅድ ሀገር በቀል እንዲሆን መሠረታዊ እርምጃ መውሰዱን ተናግረዋል። የሕብረቱ አባል ሀገራት ብሔራዊ የልማት ዕቅዶቻቸው ከአጀንዳው ጋር እየተጣጣመ መምጣቱን በማንሳት፤ የበጀት ድልድልና ፖሊሲዎቻቸው ለአፍሪካ የትኩረት መስኮች ቅድሚያ የሰጡ መሆናቸውን አስታውቀዋል። የአጀንዳ 2030 እና 2063 ግቦችን በማሳካት የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ በሀገራት መካከል ያለው ቅንጅትና ትብብር ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባም አስገንዝበዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸውን እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ አለባቸው
Apr 27, 2026 570
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2018 (ኢዜአ)፦‎ አፍሪካውያን የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የማዕድን ሀብታቸው ላይ እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከታንዛኒያ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የአፍሪካ ወሳኝ ማዕድናትን ለአረንጓዴ የኢንዱስትሪ አብዮትና ዘላቂ ልማት ማዋል" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጁት የ12ኛው የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ቀጣናዊ ቅድመ ጉባኤ ተካሂዷል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሀፊ ክላቨር ጋቴቴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ አፍሪካ እንደ ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ግራናይት እና ሌሎች የከርሰ ምድር ሀብቶችን ጨምሮ የዓለምን 30 በመቶ ማዕድናትን ይዛለች፡፡ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብቻዋን የዓለምን ከፍተኛ የኮባልት ማዕድን የያዘች መሆኑን ገልጸው፤ ይሄውም አፍሪካን የዓለም አቀፍ የኃይል ሽግግር /Energy Transition/ ማዕከል ያደርጋታል ብለዋል፡፡ አፍሪካ ዩራኒዬምና ሌሎች የከርሰ ምድር የከበሩ ማዕድናት ባለቤት መሆኗን በመጥቀስ፤ ለዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል አቅርቦት አስተዋጽኦ ከማድረግ ባለፈ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ወደ ኒውክሌር ኃይል ልማት እያመሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አፍሪካ የከበሩ ማዕድናት ባለቤት ብትሆንም አብዛኛው በጥሬ እቃ መልክ ወደ ውጭ የሚላክ በመሆኑ የአህጉሪቱ የእርስ በእርስ ግብይት ከሁለት በመቶ እንዳማይዘል ተናግረዋል፡፡ በአህጉሪቱ የማዕድናት ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን መገንባት ቢቻል በየዓመቱ ከ24 ቢሊየን ዶላር በላይ ተጨማሪ ገቢ ማግኘትና ለ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ይቻላል ብለዋል፡፡ የአፍሪካ የማዕድን ፖሊሲ ለእሴት መጨመር፣ ኢንዱስትሪ ልማትና ሁሉን አቀፍ ልማት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በአህጉሪቱ የተቀናጀ ቀጣናዊ ኢንዱስትሪ ለመገንባት ያለውን ፍላጎት በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አህጉራዊ የማዕድን ሀብቶችን ወደ ዘላቂ ብልጽግና መለወጥ ይገባል ብለዋል፡፡ በዚህም የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቀጣናዊ እሴት ሰንሰለትን በማጠናከር የማዕድን ጸጋዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚደረገው ጥረት ትብብሩን ማጠናከሩን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ዘላቂ ልማት አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካዳሪ ሲንጎ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍና አካታች ዕድገት ለማስመዝገብ የማዕድን ሀብቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ አፍሪካውያን በተፈጥሮ ሀብታችን ላይ የሚኖረን ትብብርና ተሳትፎ ስትራቴጂያዊና መዳረሻ ግብ ያለው መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና የአረንጓዴ ኢንዱስትሪ አብዮት ሽግግርን ለመፈጠር በአቅም ግንባታ ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡
አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ተምሳሌት ነበሩ
Apr 7, 2026 956
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ እሴት በተግባር ያሳዩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። ሊቀመንበሩ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ ስመጥር በሆኑት አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደሯን የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈር ቀዳጅ፣ ታላቅ ዲፕሎማት እና ህይወታቸውን ለሀገራቸውና ለአህጉሪቱ እድገት የሰጡ ጽኑ አፍሪካዊት ሲሉ አወድሰዋቸዋል። አምባሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ ለበርካታ አስርተ አመታት የዘለቀ አርአያነት ያለው ሙያዊ ስኬት ማስመዝገባቸውንና ከኢትዮጵያ ቀዳሚ ሴት አምባሳደሮች አንዷ በመሆንም ለአፍሪካውያን ሴት ዲፕሎማቶች የብርሃን ፋና መሆናቸውን አመልክተዋል። የአፍሪካን ጥቅም ለማስከበርና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የነበራቸው የማይናወጥ ቁርጠኝነት ለአህጉራዊ የጋራ ግቦች መሳካት የጎላ ሚና እንደነበረውም አውስተዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ቆንጂት በታማኝነት፣ በልዩ ብቃት እና ለጋራ የወደፊት እጣ ፈንታ የነበራቸው ጽኑ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ዲፕሎማሲ እሴቶች ያላቸውን ጽኑ አቋም ያሳየ መሆኑንም ነው ያነሱት። የአምባሳደሯ የዲፕሎማሲ አሻራ ለቀጣይ ትውልድ ዲፕሎማቶች፣በተለይም ለሴቶች፣በድፍረትና በዓላማ እንዲያገለግሉ ዘላቂ መነሳሳት ሆኖ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ስም ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ለኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ፣ እንዲሁም ለሁሉም አፍሪካውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።
ሐተታዎች
የአፍሪካዊው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣረ  ዎዴ ማያ - በአዲስ አበባ
May 6, 2026 311
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ጉባኤ በአዲስ አበባ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ይህ ጉባኤ ከሚያዚያ 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ አህጉራዊ መድረክ ነው። የአህጉሪቷ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ፤ የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ አልሟል። ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) በዲጂታል መገናኛ ብዙኅን የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና ገፅታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ አንቱታን ያተረፈ የአህጉሪቷ የዘርፉ ፈርጥ ነው። ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያለው ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበርና የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) አዲስ አበባ ገብቷል። በጉባኤው ላይ የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) መገኘትም የአፍሪካን የዲጂታል ገፅታ መቀየር የሚያስችል የአህጉራዊ ይዘት ፈጠራ ትብብርን ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ይጠበቃል። የአየር በረራ መሐንዲስ ስልጡኑ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የዲጂታል ታሪክ ተራኪነት ጉዞ በሀገረ ቻይና ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት ነበር የዩቱዩብ ይዘት ፈጠራን መሞከር የጀመረው። የመጀመሪያዎቹ የዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራዎቹም አስቂኝ የነበሩ ቢሆንም ወላጅ አባቱ የአፍሪካን በጎ ገፅታ ለዓለም ማስተዋወቅ እንዳለበት የሰጡትን ምክር ተከትሎ ጉዞውን ቀይሯል። ባህላዊ ግንኙነትን ለማጠናከር የቻይንኛ ቋንቋ ቪዲዮዎችን ያዘጋጅ የነበረው ዎዴ ማያ፤ ወደ ጋና ተመልሶ በሰራቸው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራዎቹ የሚፈለገውን ያህል ዕውቅና አላስገኙለትም ነበር። መነሻውን በአዲስ አበባ በማድረግ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉዞ በማድረግ አህጉሪቷን ለማስተዋወቅ ከሰራቸው ይዘቶች ውስጥ በሩዋንዳ የሰራው ቪዲዮ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ዕውቅናው እንዲናኝ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በእርሱ አተራረክ ማዕከላዊ ስፍራ እንዳላት የሚናገረው ዎዴ ማያ፤ የአፍሪካን ያልተነገሩ ስኬቶችና የአፍሪካዊያን ፅናት በተከታታይ ለዓለም ማስተዋወቁን ተያይዞታል። አሁን ላይ የአፍሪካን ለውጥ፣ ተስፋና ዕድሎች ለዓለም ማህበረሰብ የሚያስተዋውቁ ዘጋቢ ፊልሞችን በመስራት የአህጉሪቷን ስሁት ትርክት በመቀየር ረገድ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሰዎች አንዱ ሆኗል። በሚሊዮን የሚቆጠር ዕይታ ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞቹና የጉዞ ታሪኮችም ጊዜ ያለፈባቸው ስሁት ትርክቶችን በመሞገት የአፍሪካን ተስፋና ዕድሎች ለዓለም በመግለጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የኢትዮጵያን ዕድገትና ተስፋ ደጋግሞ የተረከው ዎዴ ማያ፤ በአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS) ወደ አዲስ አበባ መምጣቱም መድረኩን ተምሳሌታዊና ስልታዊ ያደርገዋል። ይህም የበርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) የግል ጉዞ ከመሆኑም በላይ፤ ኢትዮጵያ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጠራና የታሪክ አተራረክ ለውጦች ማዕከላዊ ሚና በተግባር ያስመሰክራል። በዚህ ጉባኤ፤ እንደ ዎዴ ማያ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች መሰባሰብ የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር በማጠናከር ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉራቸውን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ አለው። ለኢትዮጵያም የዎዴ ማያ መገኘት ሀገሪቱ ለአፍሪካ ዲጂታልና ባህላዊ ሕዳሴ ያላትን ቁርጠኝነት የበለጠ በማሳደግ አዲስ አበባን የአፍሪካ የዲጂታል ገፅታ ግንባታ ሃሳቦች መነሻነት በተግባር ያረጋግጣል።
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች
May 3, 2026 438
የቴክኖሎጂ እምርታ -ሌላው የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዞ አመላካች በሙሴ መለሰ በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው የቴክኖሎጂ ለውጥ ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ምህዳር እያሸጋገራት ይገኛል።የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ የመሰረተ ልማት እና የተቋማት ግንባታ ስራዎች ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በምታደርገው ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋንኛ ስራዎች ናቸው። ለውጡን ተከትሎ መንግስት "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን ስትራቴጂ በመቅረጽ የዲጂታላይዜሽን ስራውን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ምሰሶ አድርጎታል። የለውጡ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ ቴክኖሎጂን እንደ አንድ የኢኮኖሚ ምሰሶ በመቁጠር "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" የተሰኘውን አጠቃላይ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ተግባር ገባ።ይህ ስትራቴጂ የሀገሪቱን የዲጂታል ጉዞ ከመሰረቱ የለወጠ ሲሆን፣የመጀመሪያው ትልቅ እርምጃም የቴሌኮም ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ነበር። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጉ የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ መግባትና የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን የማዘመን ስራ የኢንተርኔት ተደራሽነት እንዲሰፋ ምክንያት ሆኗል።በተለይም የአምስተኛ ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን አስችሏታል። የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ለውጡ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ ውጤት አምጥቷል።እንደ ቴሌብር (telebirr) ያሉ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ምንም የባንክ ሂሳብ በስልካቸው ብቻ ግብይት እንዲፈጽሙ በማድረግ፣ ሀገሪቱ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር ትልቅ መደላድል ፈጥረዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ረገድ የተመዘገቡት ስኬቶችም የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ አድማስ ይበልጥ አስፍተውታል። የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ሀገሪቱ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያላትን ራዕይ ለዓለም ያሳየችበት አጋጣሚ ነው።ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት በጤናው ዘርፍ የካንሰር ህመምንና የሳምባ በሽታዎችን ቀድሞ መለየት የሚያስችሉ የኤአይ ውጤቶችን አበልጽጓል። በግብርናውም ረገድ የአፈርን ለምነትና የሰብል በሽታን በቴክኖሎጂ የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ይህም በምግብ ዋስትና ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ሌላው ትልቅ ስኬት የሀገር በቀል ቋንቋዎችን በዲጂታል ዓለም ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ የተሰሩ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ (NLP) ስራዎች ናቸው። ይህም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ እንዲካተቱና ለተጠቃሚው ምቹ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። የፋይዳ (Fayda) ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን መረጃ በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ፣ ለባንክ፣ ለጤናና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች አስተማማኝ መሠረት ጥሏል። በአሁኑ ወቅት ዜጎች እንደ ፓስፖርት ማደስ፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ግብር መክፈል ያሉ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ማከናወን መቻላቸው የለውጡ ፍሬያማነት ማሳያ ነው።የሳይንስ ሙዚየምም የወጣቶችን የፈጠራ አቅም የሚያሳይና የሀገሪቱን ቴክኖሎጂ የሚደግፍ ትልቅ አቅም ሆኗል።የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቅርቡ መጠናቀቁ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2025 ስትራቴጂው መጠናቀቁን ተከትሎ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን ገልጸዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል።ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዲጂታል 2030ን ይፋ ሲያደርጉ የነበረው ትልቁ መልዕክት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዓለም ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊና መሪ ትሆናለች የሚል ነው። ስትራቴጂው በዋናነት"የፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጋር በማቀናጀት፣ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን መፍጠር፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዲጂታል ስራ እድሎችን ለወጣቶች ማመቻቸት እና ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) አድርጎ መገንባትን እንደ ዋነኛ ግብ አስቀምጧል። ይህም ሁሉን አቀፍ የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ የመንግስት አገልግሎቶችን መቶ በመቶ ወረቀት አልባ በማድረግ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) በግብርና፣ በጤናና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ በስፋት በመተግበር የምርታማነት አብዮት መፍጠርን ያለመ ነው። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸው ኢትዮጵያ በዘርፉ የጀመረችው ስራ በአህጉራዊ ደረጃ ያለውን ተቀባይነትና የተሰጣትን ትልቅ ኃላፊነት የሚያሳይ ነው።ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት የቴክኖሎጂ ከፍታ፣ ሀገሪቱን በአፍሪካ የቴክኖሎጂ ተፎካካሪ ብቻ ሳይሆን የፈጠራ ምንጭ እንድትሆንም እያደረጋት ይገኛል። በዚህ ረገድም የቀጣዩ ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ስኬትም ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና በቴክኖሎጂ የበለጸገች ሀገር የማድረግ ራዕይን ለማሳካት እና ለሀገራዊ ብልጽግና እንደ ቁልፍ ሞተር ሆኖ ያገለግላል።
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
May 3, 2026 305
ክልሎች፤ሚያዝያ 25/2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮች በወፍ በረር ሲቃኙ ይህንን ይመስላሉ!!! 👉ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነቡትን የቶዮ ሶላር ኢነርጂ ምዕራፍ ሁለት፣ የኦሪጂን እና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎችን እንዲሁም የኤች.ዜድ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካን በይፋ መርቀዋል። እነዚህ የሶላር ፋብሪካዎች በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹሕ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን፣ የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካ ደግሞ በዓመት 900 ቶን ኦክስጅን፣ 40,000 ቶን ናይትሮጅን እና 7 ቶን ሃይድሮጅን ለገበያ ያቀርባል። ‎ይህ ክንውን የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ለማፋጠን፣ የኢነርጂ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ዘላቂ፣ የማይበገር ሁለንተናዊ እድገት ዕውን ለማድረግ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል። 👉እንቁላልን ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት የማቆየት ልምምድ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ፤ የዶሮ እንቁላል ሳይበላሽ ለሁለት ዓመት ያህል ማቆየት የሚያስችል ቴክኖሎጂን ወደ ተግባር ለማስገባት ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል። በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት ሕክምናና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ማስተዋል ብርሃን፤ ዩኒቨርሲቲው የእንቁላል ምርት ብክነትና ብልሽትን ለማስቀረት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። በዚህም እንቁላልን እስከ ሁለት ዓመት ያለ ምንም ብልሽት ማቆየት የሚያስችለውን ቴክኖሎጂን የማላመድና የማስተዋወቅ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ቴክኖሎጂው በአንድ ሊትር ውሃ ውስጥ 30 ግራም የኖራ አፈር ወይም ላይም ስቶን ጨምሮ በማዋሃድ እስከ 12 እንቁላሎችን ሳይበላሽ የሚያስቀምጥ በመሆኑ ለአርሶ አደሩ ተመራጭ ነው ያሉት። ይህም እስካሁን ባለው አንድ ትኩስ እንቁላል ሳይበላሽ መቆየት የሚችለው እስከ ሁለት ሳምንት መሆኑን ጠቁመው ቴክኖሎጂው ይሄን ችግር በመሰረታዊነት የሚቀይር ነው።፡ ቴክኖሎጂውን በስፋት በማስተዋወቅና በማላመድ ረገድም ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን በመስጠት ችግር ፈቺነቱን የማሳየት ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። 👉የአፋር ጥጥ ተስፋ ሰጪ ፀጋ! የአፋር ክልል የበርካታ የተፈጥሮ ፀጋዎች ባለቤት ነው፤ ሆኖም እነዚህን እምቅ ሀብቶች ወደ ልማት በመቀየር ከፀጋዎቹ ተቋዳሽ ለመሆን ሳይቻል ለረጅም ተቆይቷል። አሁን ግን ከፀጋዎቹ አንዱ የሆነውን ተፈጥሯዊ ጥጥ (Organic Cotton) ለማምረት ተስፋ ሰጪ ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በሰመራ በተካሄደ የውይይት መድረክም በግብርና ሚኒስቴር የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳምሶን አሰፋ፤ የአፋር ክልል ጥጥን በመስኖ ማልማት የሚቻልበት አቅም ያለው በመሆኑ ልማቱን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። በሀገራችን የጥጥ ልማትን ለማስፋፋት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው፤ ባለፈው የምርት ዘመን እንደ ሀገር በስድስት ክልሎች 110 ሺህ ሄክታር መሬት በጥጥ መልማቱን ተናግረዋል።በዚህም 79 ሺህ ሜትሮክ ቶን የተዳመጠ ጥጥ በማምረት ለኢንደስትሪዎች ማቅረብ እንደተቻለ ነው የገለፁት። 👉የሸማቹ ሸክም ይቀላል! የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን “ወደ ቀበሌ መድረስ” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ስድስት ከተሞች ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ማህበራት ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ ሲያካሄድ የህብረት ስራ ማህበራት ከእንግዲህ የሸማቹን ሸክም ሊያቀሉ ይገባል የሚል ሀሳብ ተነስቷል። በሀዋሳው በተካሔደው የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ላይ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባለፉት ስምንት ዓመታት በተለያዩ መስኮች የበለጸገችና ህብረ ብሔራዊት ሀገር ለመፍጠር ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን አንስተዋል። በተከናወኑ ተግባራትም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን አክለዋል። የመንግስትን፣ የግሉ ዘርፍንና የዜጎችን የካፒታል አቅምና ዕውቀትን ደምረው የያዙት የህብረት ስራ ማህበራት ግብርናውን በማሻገር የአርሶና አርብቶ አደሩን ህይወት በመቀየር ረገድ ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልፀው የፋይናንስ አቅርቦት ችግርን በመፍታትና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር የሸማቹን ህብረተሰብ ሸክም ያቀላሉ ተብሎ እንደሚታመንም አስረድተዋል። 👉ምርምር ለቀጣናዊ ትስስር በጅማ ዩኒቨርሲቲ "ቀጠናዊ ሰላምና ትብብር ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ባለችበት ቀጣና የሚታዩ ፍላጎቶችን ለማሟላትና ተግዳሮቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለመፍታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ጥናቶች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ ተነስቷል። በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጦሽኔ ቀጣናውን በልማት ለማስተሳሰር በሚደረግ ጥረት የትምህርት ተቋማቱ የጥናትና ምርምር ድጋፍ ከፍተኛ ሚና አለው ያሉ ሲሆን ለዚህም ተቋማቱ ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያሳድጉ እና ማህበራዊ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚያግዙ የፖሊሲ መነሻ ሀሳቦችን በጥናትና ምርምር እንዲያፈልቁ አሳስበዋል። የሚወጡ ጥናቶች በቀጣናው በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ እየተከሰቱ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሊሆኑ እንደሚገባ የተጠቀሰ ሲሆን ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራን በመተግበር እያከናወነች ያለችው ተግባር በተመክሮነት ቀርቦ አድናቆትን አስገኝቶላታል። 👉ሻይ ቅጠል አሁን አሁን አርሶ አደሩ በተለያዩ ኢንሼቲቮች በሚከናወኑ የግብርና ልማት ትግበራዎች ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ ይገኛል። በርካታ አርሶ አደሮች በሻይ ቅጠል ልማት ኢንሼቲቭ በመሰማራት ገቢን ከማሳደግ ባለፈ ለሌሎችም ሰፊ የስራ ዕድል እየፈጠሩ ይገኛሉ። በጅማ ዞን የሻይ ቅጠል ልማትን ከማስፋፋት ባለፈ የበያ ትስስር የመፍጠርና ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለፋብሪካ ለማቅረብ ለአርሶ አደሩ ግንዛቤ እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል። የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም፤ በዞኑ የሻይ ቅጠል ልማትን በኢኒሼቲቨን መልክ በመተግበር የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድል እየተፈጠረ ነው። ዘንድሮም ስራውን ለማስቀጠል በተመረጡ 6 ወረዳዎች በመጪው ክረምት የሚተከሉ 50 ሚሊዮን ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን ህዝብን በማሳተፍም ወደ 2 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬትን ለመሸፈንም ታስቧል። ጥቅሙ የገባቸው አርሶ አደሮችም የሰብል ልማቱን ለጊዜው ተወት በማድረግ በሻይ ቅጠል ልማት ላይ እየተሳተፉ እንደሆነ ይናገራሉ። በዞኑ የሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ አርሶ አደር ሲራጅ ሼክ ከድር በሻይ ቅጠል ልማት ላይ መሳተፍ ከጀመሩ ወዲህ ገቢያቸው መጨመሩን ተናግረዋል። አርሶ አደር ሱልጣን አባሞጋ በበኩላቸው ተሰማርተውበት ከነበረው የሰብል ልማት ወደ ሻይ ቅጠል ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። የአካባቢ ፀጋን ተገንዝቦ ወደ ስራ መግባት ተጠቃሚነትን እንደሚያመጣ ማሳያ ሊሆን ይችላል። 👉ተስፋዎች ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በሆሳዕና ከተማ የተካሄደው የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ደረጃ ሽግግር እውቅና መርሃ ግብር ይጠቀሳል። "የኢንተርፕራይዞች ሽግግር ለእመርታዊ እድገት" በሚል መሪ ሀሳብ የተከናወነው የዕውቅና መድረክ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት ነው የተካሄደው። እሳቸው እንደገለፁት፤ ኢንተርፕራይዞቹ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ከማምረት በተጨማሪ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠሩ ነው። በክልሉ በገጠርና በከተማ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ ከ25 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች በተለያዩ መስኮች መሰማራታቸው የተገለፀ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በጥቃቅንና በአነስተኛ ደረጃ የሚገኙ 4 ሺህ 948 ኢንተርፕራይዞችን የማሸጋገርና 495 ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን የመለየት ስራ መሰራቱም እንዲሁ። ከኢንተርፕራይዝ ወደ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሸጋገሩ አምራቾች እንደተናገሩት ሽግግሩ ስራቸውን በተሻለ ሁኔታ ለመከወን እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል። 👉ትምህርትና አርብቶ አደሩ የወፍ በረር ቅኝታችንን ስንቀጥል ጋምቤላ እንደርሳለን፤ በሳምንቱ በጋምቤላ ከተማ በተካሄደ መድረክም የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውም ተመልክቷል። በለውጡ ዓመታት የአርብቶ አደሩን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ውጤት መመዝገባቸውም እንዲሁ። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም ረገድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና የገዘፈ መሆኑም በመድረኩ መገለፁን ቅኝታችን ዳሶታል። 👉ልወቅሽ ኢትዮጵያ ሁነቶቹን ጠቅለል አድርጎ የዳሰሰው ቅኝታችን ደግሞ በስድስት ከተሞች ለማካሄድ ዕቅድ የተያዘለትና እስካሁን በጅማ፣ በሀዋሳና በደብረ ብርሃን ከተሞች የተካሄደው የ"ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ታላቁ ሩጫ" ከተሞቹን ከማስተዋወቅ የዘለለ ፋይዳውን በመርሃ ግብሩ ላይ በተላለፉ መልዕክቶቹ አሳይቷል። ለአብነት በጅማ የተካሄደው ‘ፖሊዮን በጋራ እናጥፋ’ የሚለውን የጤና ጉዳይን ያነሳ ነበር። በአዳማ ከተማ የተከናወነው ሁነት ደግሞ በመኪና ውድድር ታጅቦ የተከናወነና የቱሪዝም መስህቦችን ማስተዋወቅን ታላሚ ያደረገ ነበር። ‘’ለሀዋሳ ከፍታ እንሮጣለን’’ በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ሁነትም ከጅማና አዳማው ሁነት የተለየ እሳቤንም ሆነ መልዕክትን አልያዘም። ሁሉም ሁነቶች ከዋነኞቹ አምስት ምጣኔ ሃብታዊ አምዶች መካከል አንዱ የሆነውን ቱሪዝም ልማት በማጠናከር የማህበረሰቡን የዘርፉ ተጠቃሚነት ማላቅን ታሳቢ ማድረጋቸውን መመልከት ተችሏል። ቅኝቶቻችን በወፍ በረር ይህንን ይመስላሉ!! የሳምንት ሰው ይበለን!!!
የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር
Apr 26, 2026 682
ክልሎች፤ሚያዝያ 18 /2018 (ኢዜአ)፡-የክልሎች ቅኝት በወፍ በረር በዚህ ዝግጅታችን በሳምንቱ በክልሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በወፍ በረር የምንቃኝበት ነው። በዚህ ሳምንትም አንኳር የክልሎች ክንውኑን የሚያሳዩ መረጃዎች ቀርበዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተም! ኢትዮጵያ የበጋ መስኖ ልማት ስራ መደባኛ ስራዋ ካደረገች ወዲህ አያሌ ለውጦች እየተመዘገቡ ይገኛሉ። ባለፉት ዓመታት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በእቅድ እና በቁርጠኝነት በመከናወኑ ከውጪ የሚገባ ስንዴ ቀርቷል፤ የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጥረቱም ቀጥሏል። ከተረጂነት ወደ አምራችነት የሚደረገው ሽግግርም ዓመቱን ሙሉ በማልማት እየታጀበ ሲሆን የአንበሳውን ድርሻ የሚይዘው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሥራ ነው። በዚህ ውስጥ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አበረታች ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል። በተያዘው ሳምንት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ወሬርሶ ማሊማ፣ በጂዳ ወረዳ ሲባ ሲርቲ እና ቂምቢቢት ወረዳ ሰገሌና ደርማሙሳ ቀበሌ በኩታ ገጠም የለማ እና በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ የስንዴ ቡቃያ አስቃኝተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፎቶ ጋር ያያዙት መልዕክትም ''ይህ የበጋ የመስኖ ስንዴ ልማት በምግብ ራስን የመቻል እና የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጫ ማህተማችን ነው'' ይላል። ብሪክስ -- ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ ከሳምንቱ አንኳር ጉዳዮች መካከል በባህር ዳር ከተማ ''የብሪክስ አሁናዊ አቅሞች እና የኢትዮጵያ የልማት ትብብር ትኩረቶች'' በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀው ጉባኤ አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ከተሳትፎ ባለፈ መፍትሄ አቅራቢ በመሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑ ይታወቃል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሐመድራፊዕ አባራያ በመድረኩ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ሳትፎዋን በማሳደግ በጥናት ላይ የተመሰረቱ የተደራጁ የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅሙ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች። መድረኩም ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በፈጠራና በቴክኖሎጂ እድገት ውስጥ የራሷን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችላት የሁለትዮሽ ትብብር ጭምር የተካሄደበት፤ በብሪክስ ማዕቀፋ በተለይም በግብርና እና ስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና መሰል ዘርፎች ልምድ የተሰጠበትም መሆኑ ተመላክቷል። ማረም እና ማነጽ የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል እንዲሆኑ ለጉዳዩ ትኩረት መሰጠቱ የተገለጸውም በዚሁ ሳምንት ነው። የፌዴራልና የክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነሮች የጋራ ጉባኤ “የማረሚያ ተቋማት ለሀገር ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የማረሚያ ተቋማት የሰብዕና እና የክህሎት ግንባታ ማዕከል ሆነው እንዲያገለግሉ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከታራሚዎች የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የመሰረታዊ ፍላጎት አቅርቦት፣ ከማረሚያ ቤት የሪፎርም ሥራዎች እንዲሁም ከማረም የማነጽ ተሃድሶ ልማት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ጉባኤው በልዩ ሁኔታ የመከረበት ነው። ኢትዮጵያ ማምረቷን ቀጥላለች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና የራስን አቅም የመገንባት ታሪካዊ ጉዞ እንደቀጠለ ነው። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል "ድሬ ታምርት ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ በተዘጋጀ የአምራች ኢንዱስትሪ ኤክሲፖ ላይ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ በተደረገው ድጋፍና ክትትል እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በንቅናቄው የተዘጉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲመለሱ በማድረግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በጥራትና በስፋት እየተተኩ ነው ብለዋል። ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድም መሠረታዊ ውጤቶች ተገኝተዋል ነው ያሉት። ዘንድሮ ብቻ 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ የውጭ ሀገራት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዘርፉ ለመሰማራት መዘጋጀታቸውም ተገልጿል። ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል በኢትዮጵያ ቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ውኃ የህልውና ጉዳይ ነው። በእርግጥ ለፍጡራን ሁሉ ውኃ ህይወት ቢሆንም በእነዚህ አካባቢዎች ግን ውኃ ይበላል፤ ውኃ ይጠጣል። በሳምነቱም በአፋር ክልል ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የአይሳኢታ አፋምቦ የብዙሃን መንደር እና የአይሳኢታ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የተከናወነው ልማት የህብረተሰቡን ጥያቄዎች በተግባር ከመመለሱ በላይ፣ በየደረጃው ያለውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)፤ መንግስት የውሃ ሽፋን አነስተኛ ለሆነባቸው አካባቢዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት፣ በፕሮጀክቶች ታግዞ መስራት እንደሚገባ በጽኑ ያምናል፤ በተለይም የለውጡ መንግስት ለቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች በሰራው ስራ የውኃ ተደራሽነት በእጅጉ ማደጉን አንስተዋል። ልምድ ልውውጥ እና ተሞክሮ -ለምክር ቤቶች ሌላው ቅኝታችን በዚህ በተጠናቀቀው ሳምንት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤትና የዞን ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ መካሄዱን የዳሰሰ ነው። የጋራ የምክክር መድረኩ ዓለማ የልምድ ልውውጥና የልማት ሥራዎችን በመመልከት ተሞክሮ መለዋወጫ ነው።የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ፤ መንግስት ሕዝቡ የሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የምክር ቤቶችን አደረጃጀት ማጠናከርና የክልሉ ሕገ መንግስት ያስቀመጣቸውን ኃላፊነቶች መፈጸም ይገባል ብለዋል።የመንግስት የልማት ኢኒሼቲቮች የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል የሚያስችሉ በመሆናቸው በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው መተግበር እንዲችሉ ምክር ቤቶች ያለሰለሰ ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተመልክቷል። የጤና ልማት ስራ እስከ አክሞ ማዳን የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ በሚደረግ ጥረት የአጋር ድርጅቶች አስተዋጾ ትልቅ ድርሻ እንዳለውም የተመለከተው በዚህ ሳምንት ነው። ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጋር በመሆን በአርባ ምንጭ ከተማ ያስገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ መሰል የጤና ዘርፍ የልማት ስራዎች መንግስት በዘርፉ የያዘውን ውጥን ከማሳካት አንጻር እገዛቸው ትልቅ መሆኑን አንስተዋል።ማዕከሉ ማህበረሰቡ በቅርበት ሕክምና እንዲያገኝ ከማስቻል ባለፈ ወደ ሌላ አካባቢ ሄዶ ሲታከም ሊያወጣ የሚችለውን ወጪ ያስቀራል። ማዕከሉ የኩላሊት እጥበት ማሽኖች፣ የመድሃኒት ቤት፣ መኝታ አልጋዎችና የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች አሟልቶ የተገነባ መሆኑም ታውቋል። የከተሞች ኮሪደር- ከቱሪዝም እስክ ኮንፍረንስ ማዕከልነት በኮሪደር ልማት እጅግ ከተዋቡ እና ከደመቁ የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል ሀዋሳ አንዷ ናት። በሳምንቱ የከተማዋ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ ማጠናቀቂያ የምስጋናና ዕውቅና እንዲሁም የአራተኛ ዙር የኮሪደር ልማትና የሐይቅ ዳርቻ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄዷል፡፡ የሲዳማ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርቡ ቀጥሏል ብለዋል። በቀጣይ ለሚከናወነው የኮሪደር እና የሐይቅ ዳርቻ ልማት ስራዎች እንደሚቀጥሉ አንስተው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋና ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጎላ መሆኑን ገልፀዋል። የከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነት ለማጠናከር ሥራዎች በላቀ ፍጥነትና ጥራት መከናወናቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። ምርጫ -የዴሞክራሲ መሰረት ሳምንቱ በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ከመጠናቀቁ በፊት መራጮች የምርጫ ካርድ ወስደው ለምርጫው ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹበትም ነበር። ኢትዮጵያዊያን መጪውን ጊዜ የተሻለ የሚያደርግላቸውን መንግስት ለመመረጥ ዝግጅታቸውን በተግባር እያረጋገጡ ነው።
ትንታኔዎች
የ471 ሚሊዮን ተከታዮች ባለቤት የሆኑ የ30 ሀገራት ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሳተፉበት ታሪካዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ
May 6, 2026 328
በመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS 2026) ላይ ለመሳተፍ፣ ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡና በአጠቃላይ 321 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 61 ታዋቂ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ወደ አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል። እነዚህንም 150 ሚሊዮን ተከታዮች ያሏቸው 120 ታዋቂ ኢትዮጵያውያን የማህበራዊ ሚዲያ የይዘት ፈጣሪዎች ይቀላቀሏቸዋል። ታሪካዊው ጉባኤ ነገ እና ከነገ በስቲያ በአድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል። ጉባኤው በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ እና በኤጂኤ ቴክ ኢንተርፕራይዝ የጋራ ትብብር የተዘጋጀም ነው። በአፍሪካ የዲፕሎማሲ ማዕከል አዲስ አበባ የሚካሄደው ይህ ጉባኤ የአፍሪካን ዲጂታል የወደፊት ዕጣ ፈንታ እንደገና ለመቅረጽ ያለመ ነው። ጋናዊው ታዋቂ ዩቲዩበር እና የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅበት ስም ነው) ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገብቷል። ሴራሊዮናዊው ቦይዜ ክሪሽ፣ ቤኒናዊቷ ሬጌ ቦይዘር፣ ሴኔጋላዊው ጃው ኬቹፕ እና ስዊዛላንዳዊው ጎጎ እስዋቲኒ ኤምኤም ሌሎች ለጉባኤው የገቡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽእኖፐ ፈጣሪዎች ናቸው። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎቹ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል። ጉባኤው በአፍሪካ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የሚሰባሰቡበት፣ ስለራሳቸውና ስለ አፍሪካ የሚናገሩበት፣ እንዲሁም ስለ ይዘት ፈጠራና ስለሚገጥሟቸው ተግዳሮቶች የሚወያዩበት መድረክ ነው። ይህም ተጽእኖ ፈጣሪዎቹን በአንድ መድረክ የማገናኘት ትልቅ አጋጣሚን ፈጥሯል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በመጠቀም የይዘት ፈጣሪነት የወደፊት ሁኔታ፣ የአፍሪካ አዎንታዊ ገጽታን መገንባት እና የዲጂታል ተጽዕኖን ከአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ ጋር ማጣጣም በሚሉ ጉዳዮች ላይ ሶስት የከፍተኛ ደረጃ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ። ጉባኤው "በችግር ላይ የተመሰረተ" ዘገባን በእውነተኛ የአፍሪካ የዕድገት ታሪኮች ለመተካት የታለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑም ተመልክቷል። የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ የኢትዮጵያን ቱሪዝም በከፍተኛ ሁኔታ የማስተዋወቅ እድሉ ሰፊ ነው። እነዚህ የይዘት ውጤቶች የአፍሪካን መልካም ገጽታ ለዓለም፣ የኢትዮጵያንም መልካም ገጽታ ለአፍሪካውያን ማሳየት የሚችሉ ናቸው። ጉባኤው ሐሙስ ዕለት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚጀመር ሲሆን፣ ከ470 ሚሊዮን በላይ የዲጂታል ተከታዮች አይኖች በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ላይ አርፈዋል። ይህም አፍሪካ የራሷን ታሪክ ራሷ መተረክ የጀመረችበት አዲስ ዘመን ማሳያ ሆኗል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
May 2, 2026 642
ከሚያዝያ 18 እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአዲስ አበባ በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘውን "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የጎበኙ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ይህ ፋብሪካ በ2025 ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ያድርጉ ፎረም (Invest in Ethiopia Forum) አማካኝነት በተፈረመው ስምምነት መነሻ በ100 ሚሊየን ዶላር የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ የተቋቋመ ነው ብለዋል። ‎በውጤታማ ድጋፍ እና ክትትል በስድስት ወራት ብቻ እውን የሆነው "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻ ዘመናዊ ማሽኖች እና በቴክኖሎጂ የተዋቀረ መሆኑን ገልጸው፣ ማምረቻው ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድልም ፈጥሯል ነው ያሉት። ‎በመጀመሪያ ምዕራፍ 2 ጌጋዋት ዓመታዊ የማምረት ዐቅም ያለው ፋብሪካው የኢትዮጵያን የኃይል ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ከታዳሽ ኃይል ለማድረግ ለተጀመረው ሀገራዊ ርዕይ እውን ለማድረግ ተደማሪ ዐቅም ፈጥሯል ሲሉም ተናግረዋል። በተጨማሪም በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ የሚገኘውን የጫማ ማምረቻ እና ንዑስ የኤሌክትሪክ ጣቢያን ተመልክቻለው ብለዋል በመልዕክታቸው። • ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአራዳ ፓርክን መመረቃቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት አራዳ ፓርክን በመረቁበት ወቅት፤ ፓርኩ አዲስ አበባን ለመለወጥ ያለንን ርዕይ በተግባር ያሳየንበት አንዱ ሥራችን ነው ብለዋል። ቀደም ሲል ተዘንግቶና ለአደጋ ተጋልጦ የነበረው የአራዳ አካባቢ፤ ዛሬ ተመልሶ ተገንብቶ አስደናቂ የከተማ አካል መሆን ችሏል ሲሉም ገልጸዋል። ‎ኢትዮጵያ ለእኛ በምናብ የምትሳል ህልም ብቻ ሳትሆን በተግባር የምትገነባ እውነታ ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ጤናማ፣ ጽኑ፣ ለመጭው ትውልድ ተስፋን ከተጨባጭ ሀብት ጋር የምትሰጥ፣ በአፍሪካ መሪ፣ በዓለም መድረክ ደግሞ ተወዳዳሪ የሆነች ሀገር እየገነባን እንገኛለን ብለዋል። በየቀኑም ተስፋን ወደ እውነታ የመለወጥ ተግባራችንን እንቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል። • ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተገኝተው ሐሳባቸውን ያጋሩበት “የማኅበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀውና በማኅበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የቀረቡበት የምክክር መድረክ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‎የማኅበራዊ ዘርፍ ግንባታ እንደ ሌሎች መሠረተ-ልማቶች ውጤቱ ወዲያው የሚታይና የሚጨበጥ ባይሆንም፤ ለሀገር ዘላቂና ወሳኝ መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በሚገጥሟት ተግዳሮቶች ሳትገደብ ከሚገመተው በላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተገነባች መሆኗን ገልጸው፤ ምንም እንኳ የዐቅም ውስንነቶች ቢኖሩብንም ለማሻሻል ያልተሞከረ የማኅበራዊ ዘርፍ የለም ሲሉም አስረድተዋል። ‎በየዘርፎች የታለመው ሁሉ በተግባር እንዲተረጎምና ተገቢውን ዓላማቸውን እንዲያሳኩ ብዙ ሥራ ይጠበቅብናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም አንድ እጅ ብቻውን ማጨብጨብ እንደማይችል ሁሉ፤ መንግሥት የሚጀምራቸውን ሥራዎች ሌላው የማኅበረሰብ ክፍል እንደ አንድ ባለ ድርሻ ኃላፊነት ወስዶ በጋራ መቆም እንዳለበት አስገንዝበዋል። • የሞዛምቢክ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት የሞዛምቢክ ፕሬዚዳንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በክብር ተቀብለዋቸዋል። የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጋራ ልማትና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ትርጉም ባለው መልኩ ሊለውጡ የሚችሉ ተጨባጭ ሥራዎችን ቅድሚያ የሰጠ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለእውነተኛ አፍሪካዊ አጋርነት ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ መሆኑንም አስረድተዋል። ከዚያም ባደረጉት ቆይታ ዘላቂ እና ተጨባጭ ለውጥ ለሚያመጣ አጋርነት መሠረት የጣለ ፍሬያማ የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በስትራቴጂካዊ ዘርፎች ያለንን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩና የአሠራር ማዕቀፍ የሚሆኑ ልዩ ልዩ የመግባቢያ ሠነዶችን ልውውጥ አካሂደናል ብለዋል። • የበጋ መስኖ እርሻ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የበጋ መስኖ እርሻ በምግብ ራሳችንን ለመቻል በሚደረገው ጉዞ ውስጥ የጸና መሠረት የጣልንበት ምዕራፍ ነው ብለዋል። ‎የውኃ ሀብታችንን በአግባቡ በመጠቀም፣ ባልተቋረጠ ጥረት እና ቁርጠኝነት፣ የመልማት ጉዟችን አስተማማኝና ዘላቂ የሆነ የምግብ ዋስትና ወደምናረጋግጥበት ብሩህ ተስፋ እንደሚያሸጋግረን ጥርጥር የለውም ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሳለፍነው ሳምንት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሆሞሻ ወረዳ የሚገኘውን ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት ጎብኝተዋል። ጉብኝታቸውን ተከትሎም፤ ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት በኢትዮጵያ የግሉን ዘርፍ ያሳተፈ የግብርና ሥራ እንዲስፋፋ ለሚደረገው ሥራ አንድ ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ በግል ባለሀብት እየለማ ያለው የግብርና ሥራ እንደ ሶላር ያሉ የኃይል አማራጮችን እና የከርሰ ምድር ውኃን በመጠቀም በመስኖ በማልማት ኢትዮጵያ ለጀመረችው የግብርና ልማት እና የገጠር ሽግግር ሰፊ አስተዋጽኦ ያበረክታል ሲሉም ገልጸዋል። በተመሳሳይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግራናይት የሚያመርተውን የኦርላመንት (3ኤም) ማርብልና ቴራዞ ማኑፋክቸሪንግ የሥራ እንቅስቃሴ የጎበኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት የግሉ ዘርፍ በማዕድን ልማት ላይ በስፋት እንዲሳተፍ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ፣ ማበረታቻና ድጋፍ እንዲህ ያሉ ተጨባጭ ውጤቶችን እያመጣ ነው ብለዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከወርቅ እስከ ግራናይት በተፈጥሮ የታደለ መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ፀጋ ለሀገር ብልጽግና ለማዋል የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ይበልጥ እንዲጠናከሩ የፌደራል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።
ባሳለፍነው ሳምንት …
Apr 25, 2026 734
ከሚያዝያ 11 እስከ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል … • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር መምከራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙ እና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። በሁለቱ ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥን ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብር እና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል ሲሉም ገልፀዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላ ጋር መምከራቸው ነው። በዚሁ ወቅትም፤ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር መክረናል ብለዋል። በተመሳሳይም ከፕሬዚዳንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት ይዘው ከመጡት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማር ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅትም በሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብር ተወያይተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። እንዲሁም የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅትም፤ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል ብለዋል። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሠራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች ሲሉም አስታውቀዋል። • በኢትዮጵያ የበቆሎ መስኖ ውጤታማነት ባሳለፍነው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ትኩረት ሰጥተን እየሠራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ሥራ፤ ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል ማለታቸው ይታወሳል። የተገኘው ጅምር ውጤትም፤ ኢትዮጵያ የምግብ ዕርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን ዕውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል። • መሶብ የሞባይል አገልግሎት መመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት፤ ካቀድናቸው አምስት የልማት ምሰሶዎች መካከል ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሠራን ነው ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመሶብ አገልግሎት የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የስራውን ውጤታማነት ያረጋገጠ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰራሩን ይበልጥ መስፋፋት አስፈላጊነትም ገልጸዋል።ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የተቀናጁ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ አንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በተመሳሳይ በዚሁ ጉዳይ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባጋራው መረጃ ዛሬ ሥራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፤ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው ብሏል። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፤ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሠራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሥርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ገልጿል። ‎አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ሥርዓት እንዳለውና የተለያዩ የክፍያ አማራጮች ማካተቱንም አመላክቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደኅንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል፤ መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት፣ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣ ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የሕክምና ምርመራ ማድረግ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣ የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን፣ የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። ‎በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሔ ይሰጣል። • የ100 ቀናትና የ9 ወራት የመንግሥት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ ባሳለፍነው ሳምንት የሥራ ዘመኑ 3ኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በዚሁ ወቅትም፤ ‎የቀየስነው አዲሱ የኢኮኖሚ አካሄድ በአጭር ጊዜ ትግበራ ጠንካራ ባለሁለት አሃዝ የዕድገት ሂደትን አስመዝግቧል ብለዋል። ጥረቶቻችን የበለጠ ጽኑ፣ ተወዳዳሪ እና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ያለንን አቋም እና የመተግበር ዐቅም ያሳያሉ ሲሉም አስገንዝበዋል። • ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ስለ 3ኛው 100 ቀን አፈጻጸም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት፤ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛው የ100 ቀን አፈጻጸም ሪፖርት ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ተገምግሟል። በዚሁ ወቅትም አቶ ተመስገን፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ናት፤ የሚገባትም ትልቅ ሥፍራ ነው፤ እኛ ደግሞ የዚህ ታሪክ ሠሪዎች የመሆን ዕድል በእጃችን ላይ ነው ሲሉ አዝገንዝበዋል። በኮሪደር ልማት፣ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችና በዲጂታል ኢትዮጵያ ዘርፍ የተካሄደው የመሠረተ-ልማት አብዮት የሀገራችንን እንዲሁም የከተሞቻችንን ገጽታና አገልግሎት ቀይሯል ብለዋል። በስንዴ ልማትና በሌማት ትሩፋት አማካኝነት የተረጅነትን ቀንበር ሰብረን ወደ ምግብ ሉዓላዊነት እየተጓዝን ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዲፕሎማሲው መስክም ኢትዮጵያ ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት አጋርነት በመሸጋገር፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ተደማጭነቷን ወደ ላቀ ምዕራፍ አሳድጋለች ብለዋል። • የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች ባሳለፍነው ሳምንት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ፤ በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች፣ በሀገራችን የዩሪያ ማዳበሪያ ማምረቻና ማቀነባበሪያ ፋብሪካን የሚመለከት የኢንቨስትመንት ማበረታቻና ጥበቃ ስምምነት፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶች የሳይበር ደኅንነት ረቂቅ አዋጅ፣ በሥድስት ዓለም አቀፍ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እሳት እና ሌሎች ቅጽበታዊ አደጋዎች አገልግሎት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ መክሮ በማጽደቅ ውሳኔዎችን አሳልፏል። • ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች ብሎ ባጋራው መረጃ፤ በመሠረተ-ልማት (የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት)፣ በዲጂታል መሳሪያዎች (ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም)፣ በዲጂታል መንግሥት (በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2 ሺህ 260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትሕ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ) የሚሉትን አንስቷል። በተጨማሪም በዲጂታል ክኅሎት (‎5 ሚሊየን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በዕውቀትና በፈጠራ ማብቃት፣ በተቋማት ግንባታ (‎ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር)፣ በሕግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት (በፋይዳ መታወቂያ ከ40 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት) የሚሉት ጉዳዮችን ጠቅሷል። • የልማት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃ፤ በአረንጓዴ ዐሻራ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን አስታውቋል። ሀገራዊ የስንዴ ልማትን በተመለከተም ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል ብሏል። ‎‎ከሌማት ትሩፋት አንጻርም፤ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው፤ የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል ሲል ገልጿል። ዲጂታል ኢትዮጵያን አስመልክቶም፤ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው ብሏል። ‎‎የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማትም፤ የከተሞች መሠረተ-ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው ያለው ጽሕፈት ቤቱ፤ ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ ታምርት አኳያም፤ የማምረት ዐቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው ብሏል። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ስለመሆኑም አመላክቷል። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራ እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ሲልም በአጽንዖት ገልጿል።
ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ጤና ከሀገር በቀል ስኬት ወደ አህጉራዊ መሪነት
Apr 23, 2026 681
(በሙሴ መለሰ) ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ እያከናወነች ያለችው ስራ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂካዊ የሆኑ ተቋማዊና የፖሊሲ መሰረቶች ተጥለዋል። የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መቋቋም ለሀገራዊ ችግሮች በቴክኖሎጂ የታገዘ መፍትሄ ለማግኘት ትልቅ አቅም የፈጠረ ሲሆን፣ ብሄራዊ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፖሊሲ ተቀርጾ መጽደቁ ደግሞ የዘርፉን ልማትና አጠቃቀም በተደራጀ መንገድ ለመምራት አስችሏል። እነዚህ እርምጃዎች ሀገሪቱ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እና 2030 ስትራቴጂ ውስጥ ቴክኖሎጂውን እንደ ቁልፍ የለውጥ አቅጣጫ እንድትጠቀም በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የቴክኖሎጂ ሽግግሩን ዘላቂ ለማድረግም በሰው ኃይል ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። በአሁኑ ወቅት አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በኮዲንግ፣ በዳታ ሳይንስ እና በክህሎት ለማሰልጠን የተጀመረው ግዙፍ ፕሮግራም የለውጡ አንቀሳቃሽ ኃይል እየሆነ ነው። ከዚህም ባለፈ፣ በአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ እንዲገነባ መታቀዱና በዚህ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባልነት ውስጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት እንዲሳተፍ መወሰኑ፣ ሀገሪቱ ቴክኖሎጂውን ለውሳኔ ጥራትና ለምርምር በከፍተኛ ደረጃ እየተጠቀመችበት መሆኑን ያሳያል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ እንደገለጸው፣ ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በሹመት ደብዳቤው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ AI ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ ማድረጉ ተመልክቷል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አክሎ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የAI አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል እና በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ለሀገራዊ ለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት መሆናቸውን ጽህፈት ቤቱ በዝርዝር አስፍሯል። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የAI ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የተያዘው ሥራ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክርም ተገልጿል። ይህ አህጉራዊ እውቅና በተለይ በጤናው ዘርፍ የታዩ ውጤቶችን ያካትታል። ኢትዮጵያ በኤአይ የታገዘ ዲጂታል ኤክስሬይን ለሳንባ ነቀርሳ ምርመራ ካዋሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። በተጨማሪም የ"HEP Assist" መተግበሪያን በሙከራ ደረጃ በማስጀመር፣ በገጠር የሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ውስብስብ ምልክቶችን ሲያዩ ሙያዊ የሕክምና ውሳኔ እንዲሰጡ ድጋፍ እየተደረገ ነው። እነዚህ የዲጂታል ጤና ስራዎች በ7 ክልሎችና በ15 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ መጀመራቸው፣ ቴክኖሎጂው በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የአገልግሎት ልዩነት ለማጥበብ ያለውን ፋይዳ ያሳያል።   በአጠቃላይ፣ የኤአይ ቴክኖሎጂ በጤናው ዘርፍ ከሚሰጠው የጡት ካንሰር፣ የአንጎል እብጠትና የቆዳ በሽታዎች ምርመራ ባለፈ፣ በግብርና፣ በፋይናንስና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥም በስፋት እየገባ ይገኛል። በ2030 በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ሆስፒታሎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል አገልግሎት ለመቀየር የተቀመጠው ግብ፣ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የጀመረችውን የቴክኖሎጂ ነጻነትና የመሪነት ጉዞ ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓት በጤና፣ በግብርና እና በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥ ለውጥ እያመጣ ይገኛል። በጤናው ዘርፍ እንደ ካንሰር እና ሳንባ ነቀርሳ ያሉ በሽታዎችን ቀድሞ በመለየት የህክምና ጥራትን ሲያሻሽል፣ በግብርናው ደግሞ የሰብል ተባዮችንና የቡና በሽታዎችን በመለየት ምርታማነትን እያሳደገ ነው። ከዚህ ባለፈም ቴክኖሎጂው በመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥ እና በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ሰፊ የመረጃ ትንታኔዎችን በፍጥነት በማከናወን፣ የሥራ ፍጥነትን እና የውሳኔ አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ ይገኛል። የዘርፉ ፋይዳ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባለፈ የሀገሪቱን የዲጂታል ሉዓላዊነት እና የሰው ኃይል አቅም በመገንባት ላይ ያተኩራል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶችን በኮዲንግ እና በዳታ ሳይንስ በማሰልጠን እንዲሁም የፈጠራ ማዕከላትን (Startups) በመገንባት፣ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በሌሎች ላይ ጥገኛ ከመሆን ወጥታ የራሷን የዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት እየጣለች ትገኛለች። ይህም በአህጉር ደረጃ ለሚደረጉ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች እንደ አርአያ በመሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ ፍትሃዊነት የመጠቀም ጥቅል ፋይዳው የጎላ እንዲሆን አድርጎታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሹመት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ ያጎላል። በተጨማሪም ሹመቱ የኢትዮጵያ ተሞክሮ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ማግኘቱንና አፍሪካ በኃላፊነትና በፍትሐዊነት በታጀበ የኤአይ አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንድትሆን የመሪነት ሚናዋን እንድትወጣም ያደርጋታል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 4663
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 3083
በዮሐንስ ደርበው በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 8875
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 7359
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 62314
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 55730
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 36202
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33805
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 28405
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 27736
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 27229
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 26699
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 62314
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 55730
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 36202
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 33805
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ
Apr 25, 2026 957
አዲስ ምዕራፍ- ከዜጎች ደጃፍ እስከ እጅ ስልክ በቁምልኝ አያሌው በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ውስጥ የመንግሥት አገልግሎት ጥራት ከሰው ልጅ የደም ዝውውር ጋር ይመሰላል። በሌላ በኩልም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ የዜጎች የሞራልና የፍትሕ ልዕልና መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። መንግሥት ለዜጎቹ የሚያቀርባቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ጥራት፣ ፍጥነትና ፍትሐዊነትም የሀገርን ፖለቲካዊ መረጋጋትና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የሚበይኑ መጋቢዎች ናቸው። ታዋቂው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምሁር ፍራንሲስ ፉኩያማ እንደሚሉት፤ "የመንግሥት ተቋማት ብቃት (State Capacity) ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዴሞክራሲ መረጋጋት መሠረት ነው።" መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት የሕዝብ አመኔታን በመጨመርና ማህበራዊ እኩልነትን በማስፈን ለዘላቂ ሰላም የማይተካ ሚና ይጫወታል። ይህም ሀገርን በኢኮኖሚ ለማሳደግና ለማበልጸግ በሚደረገው ርብርብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ሌላኛው የኢኮኖሚክስ ምሁር ጆሴፍ ስቲግሊዝ በበኩላቸው፤ "ውጤታማ መንግሥት ማለት ዜጎቹን በግልጽነትና በተጠያቂነት የሚያገለግል፣ በሂደቱም የህዝብ አመኔታን መገንባት የሚችል ነው" ሲሉ አጽንኦት ይሰጣሉ። በአንፃሩ፤ የአገልግሎት ክፍተትና የአስተዳደር ጉድለት ለሀብት ብክነት፣ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር በመክፈት ዜጎችን ለከፍተኛ ምሬት በማጋለጥ አመኔታን ያሳጣል። ይህንን እንግልት ለማቃለል ሀገራት አገልግሎትን የሚያዘምን ፈጣንና ቀልጣፋ የዲጂታል ሥርዓት እየዘረጉ ይገኛል። ኢትዮጵያም ይህንን መርህ በመከተል ዘገምተኛ አሰራር ከወለደው የ"እጅ መንሻ" (ሙስና) ልምምድ በመላቀቅ ዘመናዊና ግልጽ የዲጂታል ሽግግርን በማፋጠን ላይ ትገኛለች። ይህም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባትና ሉዓላዊነትን የሚያጎናጽፍ ወሳኝ የልማት ምኅዳር እየፈጠረ ነው። የመደመር መንግሥት ዕሳቤ፤ በተቋማት ግንባታና አገልግሎት ጥራት!! በመደመር ፍልስፍና ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት ተደርገው ይወሰዳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው ገፅ-129 እንዳሰፈሩት፤ ''የመደመር መንግሥት ከውስብስብ ቢሮክራሲ ተላቀው የመደመር ለውጥ የሚያመጡ ተቋማት ውቅር ነው። በመሆኑም ተቋማት ከተለመደ ''የሥራ ሂደት መር'' አካሄድ መላቀቅ ይጠበቅባቸዋል። አደረጃጀታቸውንም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያገኙ ወደሚረዳቸው አደረጃጀት መሸጋገር አለባቸው። ለመደመር መንግሥት ሕዝቡን ማገልገል ከቢሮክራሲ በላይ ነው'' በሚል አስገንዝበዋል። ለዚህም ነው ተቋማት የሰውን ልጅ አቅምና ዕውቀት አቀናጅተው ለጋራ ዓላማ የሚያውሉ ሕያው መዋቅሮች ናቸው የሚባለው።   በመደመር ዕሳቤ ጠንካራ ተቋማት ማለት በግለሰቦች ፍላጎትና ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ ይልቁንም በሕግና በሥርዓት የሚመሩ መሆን አለባቸው። በመደመር መንግሥት መፅሐፍ ገፅ-130 እንደሰፈረው፤ ''በየተቋማት ያሉ የመንግስት ሠራተኞች ሕዝቡን ከቢሮክራሲው በላይ የሚመለከቱ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አገልጋይነትን የተላበሱ መሆን ይጠበቅባቸዋል።'' መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ይህንን ዕሳቤ በተግባር የሚተረጉም ነው። ግለሰባዊ ንክኪን በመቀነስና አሰራርን በቴክኖሎጂ በመተካት ተቋማት ከግለሰቦች መልካም ፈቃድ ይልቅ በሥርዓት ወደሚመራ ተቋማዊ ብቃት መሸጋገርን ያሳያል። የአገልግሎት ጥራትና የዜጎች ክብር በመደመር መንግሥት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ሰው ተኮር የልማት ነጥብ ነው። ''ለሕዝቡ ቅድሚያ የማይሰጥ አመራርም ሆነ ሠራተኛ የመደመር መንግሥት ወገን አይደለም። እንዲህ ዓይነቱን ግለሰብም ሆነ አይቶ እንዳላየ በማለፍ የማይታገል ሰው በመደመር መንግሥት ውስጥ ዕድል ፈንታ የለውም'' በሚል በመደመር መንግሥት መፅሐፍ የሰፈረው ግልፅ መልዕክትም መንግሥት የአገልጋይነት እንጂ የገዥነት መንፈስ ሊኖረው እንደማይገባ በጉልህ ያመላክታል። የአገልግሎት ጥራት መሻሻልም ዜጎች በሀገራቸው ተቋማት ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆ ያለ እንግልት የሚገለገሉበትን ምኅዳር ይፈጥራል። በተቋማት አገልግሎት የዜጋ እርካታ (Citizen Satisfaction) ዋነኛ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ ተደርጎ ይወሰዳል። በመደመር መንግስት ዕይታ የብልሹ አሰራር መታገያ ስትራቴጂ በጩኸትና በቅጣት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን አሰራርን በማዘመን ጭምር ነው። የመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ሌብነትን የማይጋብዝ ሥርዓት የፈጠረ (Systemic Prevention) ስትራቴጂክ አቅጣጫ ሆኗል።   የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማትና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመደመር መንግሥት መሠረታዊ የተቋማት ሪፎርም ትግበራን (Institutional Reform) የሚያሳዩ ናቸው። ይህም ተቋማትን ከመዋቅራዊ ሽግግርና ለውጥ ባለፈ የተቋማት ሠራተኞችን ከመንግሥት ሠራተኛነት ወደ ሕዝብ አገልጋይነት የአስተሳሰብ ለውጥ (Paradigm Shift)፣ ኋላ ቀር አሰራርን በዲጂታል የቴክኖሎጂ አማራጭ የሚተካ (Technology Integration)፣ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅርበትና ፍትሐዊነት የማዳረስ ፅንሰ ሃሳባዊ ግብን በተግባር ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ታላቅ ተግባርም ኢትዮጵያ በመደመር ዕሳቤ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና ዜጎች በመንግሥታቸው ላይ ያላቸውን አመኔታ በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ መሠረት ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይና ስትራቴጂክ ሽግግር!! ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ዘርፎች ወሳኝ የልማት ዕድሎችን ፈጥሯል። በዚህ ሰፊ መርሃ ግብር ውስጥ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ዋነኛ የብልፅግና ምሰሶ ተወስዷል። በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ-2025" ስትራቴጂ የተጀመረውና በስኬት የተጠናቀቀው ጉዞ ዛሬ ላይ ሀገሪቷን ወደ "ዲጂታል ኢትዮጵያ-2030" አሸጋግሯታል። ይህ ስትራቴጂ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበትን ምኅዳር በመፍጠር በሰው ንክኪ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችንና የአገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ረገድ ታሪክ ቀያሪ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የልማትና ዕድገት ምሁሩ አማርትያ ሴን፤ "ልማት የሰው ልጅ ምርጫና የመገልገያ አቅሙን ማስፋፊያ መሣሪያ ነው" በማለት የሚገልጹት ስለልማት ከፍ ያለ ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች የሚያጋጥሟቸውን እንግልቶች በማስወገድ ትኩረታቸውን በልማት ላይ እንዲያደርጉ በማስቻሉ፣ ይህንን የልማት ፅንሰ-ሃሳብ በተግባር እየተረጎመ ይገኛል።   የአንድ ጣሪያ በረከትና የቅልጥፍና ተምሳሌት - መሶብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 18/2017 ዓ.ም የተመረቀው የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ ለተቋማዊ ሽግግር መነሻ ሆኗል። ቁልፍ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ስር መሰባሰባቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ አሸጋግሮታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውንና ሀብታቸውን በመቆጠብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ለዘመናት የቆየውን ምሬት የሚቀለብስ የሪፎርም እርምጃ ነው። በወቅቱ ሲጀመር 12 የነበሩት ፌዴራል ተቋማት፤ አሁን ላይ 23 በመሻገር አገልግሎታቸውን እየሰጡ ይገኛል። ይህም የዜጎች እንግልት በማስቀረት ታላቅ እፎይታን ፈጥሯል። እነዚህ ተቋማት፦ የብሔራዊ መታወቂያ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን፣ ኢትዮ ፖስታ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት ናቸው። መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል ተቋማት በአንድ በማሰባሰብ የጀመረው ይህ አገልግሎት አሁን ላይ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ተደራሽ እየሆነ ነው። ይህም የመልካም አስተዳደር እጦትን የሚያቃልል ታሪክ ቀያሪ መደላድል ፈጥሯል። አዲስ መሶብ - የተንቀሳቃሽ አገልግሎት ተስፋ!! በመዲናችን ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት፣ "መንግሥት ወደ ዜጋው ይሄዳል" (Citizen-Centric Governance) የሚለውን የዘመናዊ አስተዳደር ፍልስፍና በተግባር ያሳየ ነው። በፀሐይ ኃይልና በፈጣን ኔትወርክ የታገዘው ይህ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት የስምንት ተቋማትን 36 ዓይነት አገልግሎቶች ወደ ህዝቡ ደጃፍ በማምጣት ረገድ ተምሳሌት ሆኗል።   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትባ ብትቆይም፣ የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ግን ለተገልጋዩ እውነተኛ እፎይታን ይዞ መጥቷል። የቀጣዩ ዘመን ግብ - አገልግሎትን በእጅ ስልክ!! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀጣይ አገልግሎቱን ወደ ዜጎች የእጅ ስልክ የማሸጋገር ግብ መኖሩን አረጋግጠዋል። ይህ ሽግግር ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን የዲጂታል መታወቂያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ዜጎችን በዲጂታል መታወቂያ መለየት መቻሉ የአሰራር ግልጽነትን ከመጨመሩም በላይ መንግሥት አገልግሎቱን ለማን እየሰጠ እንደሆነ በትክክል እንዲያውቅ ያስችለዋል።   ተገልጋይን አክብሮ፣ ስርቆትና "እጅ መንሻን" አስቀርቶ አገልግሎት መስጠት የባህል ለውጥ ይጠይቃል። ለዚህም ሲቪል ሰርቪሱን በማዘመን፣ ቴክኖሎጂንና የባህል ለውጥን በማቀናጀት የእጅ መንሻን ባህል የሚያስቀር መሠረት እየተጣለ ይገኛል። ለዚህ ለውጥ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋና ተቋም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የዲጂታል ልማት መርሃ ግብርና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሙስናን በማድረቅ ፍቱን መፍትሔ እየሰጡ ይገኛሉ። ይህም ሀገሪቷን ከቆየችበት የ"እጅ መንሻ" አዙሪት አውጥቶ፣ ተቋማት ለዜጎች ክብር ወደሚያሳዩበት አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯታል። ይህ ጉዞ እመርታ ነው፤ ግልጽነትን በማንገስና የህዝብን እርካታ በመጨመር የብልጽግና ጉዞውን የሚያፋጥን ነው።
ፋሲካ -አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል
Apr 12, 2026 987
በኢትዮጵያ የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው። የትንሳኤ በዓል የሚከበረው ከ55 ቀናት የጾም ወቅት በኋላ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እነዚህን ቀናት ፈጣሪያቸውን በጾምና ጸሎት ከመለመን ባለፈ ከሥጋ፣ ከወተትና መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምግቦች ታቅበው ነው የሚያሳልፉት። የትንሣኤ በዓል ከመድረሱ በፊት ያለው አንድ ሳምንት "ሰሞነ ሕማማት" በመባል ይታወቃል። የእምነቱ ተከታዮች በሰሞነ ሕማማት ኢየሱስ ክርስቶስ ያሳለፈውን መከራና ስቃይ በማሰብ በቤተ ክርስቲያን በስግደት፣ በጸሎትና በጾም በተለየ ሁኔታ ያሳልፋሉ። ምእመናን በእለተ አርብ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን ብሎ በቀራኒዮ አደባባይ የከፈለውን መከራ፣ ግርፋትና ስቅላት በማሰብ በስግደት፣ በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች ያሳልፋሉ። የትንሳኤ (የፋሲካ) በዓልም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትል ድል አድርጎ መነሳቱን ተከትሎ የሚከበር ነው። ትንሳኤው ይቅርታ፣ ለሰው ለጆች መዳን የተከፈለ ፍቅርና መስዋዕትነት ጎልቶ የሚታይበት ነው። በመሆኑም ፋሲካ ሞትን ድል በመንሳት በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በትንሳኤ የለወጠበት ለሰው ልጅም ፍቅርን በቤዛነት ተክቶ ያሳየበት ዕለት ነው። ዕለቱ ትንሳኤ ብርሀን የታየበት በመሆኑ በትንሣኤ ዋዜማ ቅዳሜ ምሽት ምዕመናን ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በጸሎትና በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርአቶች ያሳልፋሉ። የሌሊቱ ቅዳሴና ስርአተ ፀሎት ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕመናን ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ጾም ይፈታሉ። ከቅባት ምግቦች ለሁለት ወራት በመቆጠብ ያሳለፉበት ወቅት በመሆኑም በትንሳኤ ሌሊት ዶሮ በመብላት ጾማቸውን ይፈስካሉ። በበዓሉ ቀንም በነጭ የሀበሻ ልብስ ደምቀው ይታያሉ። በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥርአቱ ባለፈ የአብሮነት፣ የፍቅርንና የመተሳሰብ እሴት ያለው ነው። ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና ከጎረቤት ጋር አብሮ በመብላትና በመጠጣት የሚያሳልፉት ነው። ቤት ያፈራውን በመቋደስ በዓሉን በአብሮነት በደስታ ያሳልፋሉ። የፋሲካ በዓል ማህበራዊ ትስስር የሚገለጥበትና አብሮነት የሚደምቅበት የደስታ በዓል ነው። በተለይ በፋሲካ በዓል ለዶሮ ወጥ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ፋሲካና ዶሮ ወጥ ጥብቅ የሆነ ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው በመሆኑ አንዱ የበዓሉ ማድመቂያ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በተጨማሪ የበሬ ቅርጫ፣ በግ፣ ፍየል፣ ዳቦና ጠላ እንደየ አቅም በማዘጋጀት ይከበራል። በአንዳንዶች ዘንድም ከገብስ ብቻ የሚዘጋጅ "ኬኔቶ" የተሰኘ (ከአልኮል ነፃ የሆነ መጠጥ) በማዘጋጀት በአማራጭነት ይቀርባል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም